ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ወጪን በራስ አቅም የመሸፈን ሂደቱን አሳድጓል
Jul 13, 2025 13
አሶሳ፤ ሐምሌ 6/2017 (ኢዜአ)፦በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017 በጀት ዓመት በቅንጅት በተሰበሰበ ገቢ ወጪን በራስ የመሸፈን ሂደቱን በማሳደግ ላይ መሆኑን የክልሉ ገቢዎች ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ተፈሪ አበበ ለኢዜአ እንዳስታወቁት፤ በበጀት ዓመቱ 4 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዞ ሲሰራ ቆይቷል። በበጀት ዓመቱን በተቀናጀ አኳኋን በተሰራው ሥራም ከእቅድ በላይ አምስት ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ተችሏል ብለዋል። ከተለያዩ ተቋማት ጋር የነበረው ቅንጅታዊ አሰራር መጠናከር፣ ዘመናዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓት መስፈን እና የህግ አሰራሮች ላይ ማሻሻያ መደረጉ የላቀ አፈጻጸም እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል። ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ46 በመቶ ብልጫ እንዳለው አቶ ተፈሪ አስታውቀዋል። ክልሉ የራሱን ወጪ የመሸፈን አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ዓመት የራሱን ወጪ የመሸፈን አቅሙ ወደ 60 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። ግብር ከፋዩ ግብርን በወቅቱ የመክፈል እና የግብርን አስፈላጊነት እየተገነዘበ በመሆኑ የታክስ ማጭበርበር እና ስወራ እየቀነሰ መምጣቱን አመላክተዋል። ክልሉ ካለው የገቢ አማራጭ አንፃር መሰብሰብ የሚገባውን ገቢ አላገኘም ያሉት አቶ ተፈሪ ተጨማሪ የገቢ አማራጮች ላይ ጥናት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ ይጀምራል
Jul 13, 2025 10
ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ እንደሚጀምር የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። ምክር ቤቱ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚያካሄደው ጉባኤ በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይም ተመልክቷል። የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ለኢዜአ እንዳሉት ምክር ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤውን ከነገ ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል። ምክር ቤቱ ከነገ ጀምሮ በሚያካሂደው 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውም በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ ተናግረዋል። ከአጀንዳዎቹ መካከልም የምክር ቤቱን የ8ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ የ2017 አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2018 ረቂቅ ዕቅድና በጀት ማፅደቅ እንደሚገኙበትም አፈ-ጉባኤዋ አመልክተዋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የኦዲት መስሪያ ቤቱ የ2017 ዓ/ም አፈጻጸም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድና በጀት ቀርቦ ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተገልጿል። እንዲሁም በምክር ቤቱ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና ሹመቶች ቀርበው እንደሚፀድቁም ዋና አፈ-ጉባኤዋ ተናግረዋል።
የአውሮፓ ኃያላኑ ቼልሲ እና ፒኤስጂ የክለቦች ዓለም ዋንጫን ለማንሳት ይፋለማሉ
Jul 13, 2025 14
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ ቼልሲ እና ፒኤስጂ ዛሬ የፍጻሜ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፍጻሜው ጨዋታ ላይ ይታደማሉ። የፍጻሜው ጨዋታ 82 ሺህ 500 ተመልካች በሚያስተናግደው ሜት ላይፍ ስታዲየም ምሽት 4 ሰዓት ላይ ይካሄዳል። ቼልሲ በግማሽ ፍጻሜው የብራዚሉን ፍሉሜኔንሴን 2 ለ 0 አሸንፏል። ፒኤስጂ ሪያል ማድሪድ 4 ለ 0 በመርታት ለፍጻሜው አልፏል። ቼልሲ እና ፒኤስጂ ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 10 የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ፒኤስጂ 5 ጊዜ ሲያሸንፍ ቼልሲ 2 ጊዜ አሸንፏል። 3 ጊዜ አቻ ወጥተዋል። ሁለቱ ቡድኖች ስምንት ጊዜ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተገናኝተው ፒኤስጂ 3 ጊዜ ድል ሲቀናው ቼልሲ 2 ጊዜ አሸንፏል። በቀሪዎቹ ሶስት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርተዋል። አስደናቂው ፒኤስጂ የአሸናፊነት ስነ ልቦናው፣ የተከላከይ መስመሩ ጥንካሬ፣ የአማካይ ክፍሉ ኳስ የመቆጣጠር ብቃት እና ፈጣን የማጥቃት እንቅስቃሴው ከብዙዎች አድናቆት እያስቸረው ነው። የፓሪሱ ክለብ በክለቦች ዓለም ዋንጫ እስከ አሁን ባደረጋቸው ስድስት ጨዋታዎች አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። 16 ግቦችን ሲያስቆጥር ያስተናገደው አንድ ግብ ብቻ ነው። ቡድኑ ከስድስቱ ጨዋታዎች በአምስቱ ግብ አልተቆጠረበትም። የተከላካይ መስመር ክፍሉ ተጋላጭነት፣ የትኩረት ማጣት አጋጣሚዎች እና ግብ የመፍጠር ኃላፊነት በተወሰኑ ተጫዋቾች ላይ የተንጠለጠለ መሆኑ ፒኤስጂ እንደ ድክመት ሊነሱበት የሚችሉ ጉዳዮች ናቸው። ተጋጣሚው ቼልሲ በወጣቶች እና የመጫወት ረሃብ ባላቸው ባለክህሎቶች የተሞላ ነው። የአማካይ ክፍሉ ጥንካሬ እና ሚዛን፣ የታክቲክ ተለዋዋጭነት እና የታክቲክ ተገዢነት እንዲሁም የማጥቃት አቅም የምዕራብ ለንደኑ ቡድን የጥንካሬ መገለጫዎች ናቸው። ቡድኑ በውድድሩ ባደረጋቸው ስድስት ጨዋታዎች አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏልክ። 14 ግቦችን ሲያስቆጥር 5 ግቦች ተቆጥረውበታል። የተከላካይ ክፍሉ የአደጋ ተጋላጭነት፣ ልምድ ማነስ እና የጎል ማስቆጠር ያሉ ችግሮች አንድ ድክመት ይነሱበታል። ፒኤስጂ ከፈረንሳይ ሊግ 1፣ የፈረንሳይ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ እና የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ድሉ በኋላ አራተኛውን ዋንጫ ለማንሳት ይፋለማል። ቼልሲ ከአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ድሉ ላይ የክለቦች የዓለም ዋንጫን ለመጨመር ይጫወታል። ፒኤስጂ ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ ግምቱን ቢውሰድም ዋንጫ ካየ ወደ ኋላ ከማይለው ቼልሲ ጠንካራ ፈተና ይጠብቀዋል። የኢራን እና አውስትራሊያ ጥምር ዜግነት ያላቸው የ47 ዓመቱ አሊሬዛ ፋግሃኒ ተጠባቂውን የፍጻሜ ጨዋታው በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፍጻሜውን ጨዋታ በሜትላይፍ ስታዲየም ተገኝተው እንደሚከታተሉ ተረጋግጧል። የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ለውድድሩ ተሳታፊዎች በአጠቃይ የአንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽልማት አዘጋጅቷል። ውድድሩን የሚያሸንፈው ቡድን የ40 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽልማት ያገኛል። ለፍጻሜ ያለፉ ቡድኖች ለፍጻሜ በማለፋቸው ብቻ 30 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይበረከትላቸዋል።
በክልሉ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Jul 13, 2025 28
አዳማ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት መከናወናቸውን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ አስታወቁ። የኦሮሚያ ክልል የ2017 በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ የስራ አፈፃፀም ግምገማ የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ፣ አፈጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማንን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአዳማ መካሄድ ጀምሯል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንደገለፁት በክልሉ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል። የክልሉ መንግሥት የአርሶና አርብቶ አደሩን እንዲሁም የከተማ ነዋሪዎችን ኑሮ ህይወት ለማሻሻልና ለመለወጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በስራ እድል ፈጠራ፣ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም በማዘመን፣ ገቢን በማሳደግና የአርብቶ አደሩን ህይወት መለወጥ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት መሰራቱን ጠቅሰዋል። መድረኩ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም በጥልቀት የሚፈተሽበትና ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው ለ2018 በጀት ዓመት አቅጣጫ የሚያዝበት መሆኑን አመላክተዋል። በየደረጃው ያለው አመራርም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተገኙ አበረታች ውጤቶችን በአዲሱ በጀት ዓመት በሙሉ አቅሙ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባው አስገንዝበዋል። "አዲሱ የበጀት ዓመት ለህዝቡ ቃል የገባንበት ሁለንተናዊ የልማት መስኮች ለማሳካት በሙሉ አቅማችን የምንረባረብበት ዓመት በመሆኑ በየደረጃው ያለው አመራር ራሱን ማዘጋጀት አለበት" ሲሉም አክለዋል። ለአገልግሎት አሰጣጥ እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ብልሹ አሰራሮች፣ ሌብነት፣ ህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ፣ የጎጠኝነትና የጥቅም ጥገኝነት አመለካከቶችና አስተሳሰቦችን ለማምከን መረባረብ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በበኩላቸው የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግሥትና በፓርቲ ስራ የተሻለ ተግባር የተከናወነበት ነው ብለዋል። በዚህም ጠንካራ የመንግስትና የፓርቲ አደረጃጀትና አሰራር ለመፍጠር አበረታች ስራዎች የተከናወኑበት መሆኑንም ተናግረዋል። የቀበሌ አደረጃጀትና መዋቅር በመዘርጋት በተለይም ህዝቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል። በዚህም በክልሉ የተሻለ ሰላም በማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ማከናወን የተቻለበት መሆኑን አመልክተዋል።
ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከ19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች ተመዝግበዋል
Jul 13, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እስካሁን ከ19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች መመዝገባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ገለጹ። በኢትዮጵያ የነዋሪዎችን የመታወቅ መብት ለማረጋገጥ፣ በአገልግሎት ሰጭና ተቀባዮች መካከል መተማመን እንዲዳብር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና የተሳለጠ አሰራር ለመዘርጋት የዲጂታል መታወቂያ ገቢራዊ ተደርጓል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት በአዲስ አበባ እና በክልል የዲጂታል የመታወቂያ ምዝገባ ማከናወንና ከተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ፡፡ ይህንን ተከትሎ እስካሁን 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን ነዋሪዎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውንና ከ55 ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል ፡፡ በ2018 በጀት አመት የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን የበለጠ ለማሳደግ እቅድ መያዙንና ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡ በተለይ በክልሎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን ይበልጥ ለማስፋት ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት አመት በክልሎች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መሰራቱን እና በዚህም ውጤት መገኘቱንም አስታውቀዋል። ለዚህ ከከፍተኛ አመራሩ ጀምሮ ለስራው ትኩረት ሰጥቶ ህብረተሰቡ የዲጂታል መታወቂያ እንዲመዘገብ በማድረግ በኩል ትልቅ ተግባር ተከናውኗል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ትምህርት ማህበረሰቡ የፋይዳ ዲጂታል ትግበራ በትምህርት ቤቶች ውጤታማ እንዲሆን ያከናወነውን ተግባር በተሞክሮነት ወደ ክልሎች የማስፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለጻ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት የዲጂታል አገልግሎቱን ለማሳለጥና ጠንካራ የሆነ የማንነት አስተዳደር ስርዓት ለመፍጠር እያገዘ ይገኛል፡፡
ፖለቲካ
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ ይጀምራል
Jul 13, 2025 10
ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ እንደሚጀምር የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። ምክር ቤቱ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚያካሄደው ጉባኤ በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይም ተመልክቷል። የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ለኢዜአ እንዳሉት ምክር ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤውን ከነገ ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል። ምክር ቤቱ ከነገ ጀምሮ በሚያካሂደው 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውም በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ ተናግረዋል። ከአጀንዳዎቹ መካከልም የምክር ቤቱን የ8ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ የ2017 አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2018 ረቂቅ ዕቅድና በጀት ማፅደቅ እንደሚገኙበትም አፈ-ጉባኤዋ አመልክተዋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የኦዲት መስሪያ ቤቱ የ2017 ዓ/ም አፈጻጸም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድና በጀት ቀርቦ ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተገልጿል። እንዲሁም በምክር ቤቱ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና ሹመቶች ቀርበው እንደሚፀድቁም ዋና አፈ-ጉባኤዋ ተናግረዋል።
በክልሉ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Jul 13, 2025 28
አዳማ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት መከናወናቸውን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ አስታወቁ። የኦሮሚያ ክልል የ2017 በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ የስራ አፈፃፀም ግምገማ የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ፣ አፈጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማንን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአዳማ መካሄድ ጀምሯል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንደገለፁት በክልሉ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል። የክልሉ መንግሥት የአርሶና አርብቶ አደሩን እንዲሁም የከተማ ነዋሪዎችን ኑሮ ህይወት ለማሻሻልና ለመለወጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በስራ እድል ፈጠራ፣ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም በማዘመን፣ ገቢን በማሳደግና የአርብቶ አደሩን ህይወት መለወጥ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት መሰራቱን ጠቅሰዋል። መድረኩ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም በጥልቀት የሚፈተሽበትና ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው ለ2018 በጀት ዓመት አቅጣጫ የሚያዝበት መሆኑን አመላክተዋል። በየደረጃው ያለው አመራርም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተገኙ አበረታች ውጤቶችን በአዲሱ በጀት ዓመት በሙሉ አቅሙ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባው አስገንዝበዋል። "አዲሱ የበጀት ዓመት ለህዝቡ ቃል የገባንበት ሁለንተናዊ የልማት መስኮች ለማሳካት በሙሉ አቅማችን የምንረባረብበት ዓመት በመሆኑ በየደረጃው ያለው አመራር ራሱን ማዘጋጀት አለበት" ሲሉም አክለዋል። ለአገልግሎት አሰጣጥ እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ብልሹ አሰራሮች፣ ሌብነት፣ ህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ፣ የጎጠኝነትና የጥቅም ጥገኝነት አመለካከቶችና አስተሳሰቦችን ለማምከን መረባረብ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በበኩላቸው የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግሥትና በፓርቲ ስራ የተሻለ ተግባር የተከናወነበት ነው ብለዋል። በዚህም ጠንካራ የመንግስትና የፓርቲ አደረጃጀትና አሰራር ለመፍጠር አበረታች ስራዎች የተከናወኑበት መሆኑንም ተናግረዋል። የቀበሌ አደረጃጀትና መዋቅር በመዘርጋት በተለይም ህዝቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል። በዚህም በክልሉ የተሻለ ሰላም በማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ማከናወን የተቻለበት መሆኑን አመልክተዋል።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት በወታደራዊ ቴክኖሎጂ ፈጠራ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ነው - ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር)
Jul 12, 2025 160
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በወታደራዊ ቴክኖሎጂ ፈጠራ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ እንደሚገኝ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ እና በኃብት አስተዳደር እንዲሁም በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። መንግሥት ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታ እንዲሁም ወታደራዊ ቴክኖሎጂ ማፍለቅና ማምረት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በእውቀት፣ በዓላማ እና በሙያዊ ክህሎት የታነጹ ጀግና የሰራዊት አባላት እና ቴክኖሎጂ ፈጣሪዎችን እያፈራን ነው ብለዋል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት በወታደራዊ ቴክኖሎጂ ፈጠራ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲም የሰለጠነ የሠራዊት አባላትንና ሲቪል አመራር በማፍራት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። የሠራዊቱን የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ብቃት ለማላቅ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይም ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ ማገዝ የሚችሉ ብቁና ሥነ-ምግባር ያላቸውን ሙያተኞች እያፈራ መሆኑን ጠቁመዋል። ዩኒቨርሲቲው ለሀገርና ለመጪው ትውልድ የሚሻገር ስራ መሥራቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸው፥ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎትን በማስፋት እንዲተገብርም ተናግረዋል። በዘመናዊ የሠራዊት ግንባታ ሂደት እውቀትና ቴክኖሎጂ መሠረታዊ መሆኑን አንስተው ለዚህም ዩኒቨርሲቲው ከዚህ አኳያ አመርቂ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተመራቂዎች በታማኝነት፣ በቅንነትና በስነምግባር ሀገራቸውን ማገልገል እንዳለባቸውም አፅንኦት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ፤ ዩኒቨርሲቲው በእውቀትና በክህሎት ብቁ የሆነ የሰው ኃይል እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የመከላከያ ሰራዊቱን የተልዕኮ አፈጻጸም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ወታደራዊና ሲቪል አመራሮችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገርን የሚያሻግሩ ሥራዎች በመስራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው የመከላከያን የሰለጠነ የሰራዊት ግንባታ በማገዝ ላይ መሆኑንም አንስተዋል። ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባቸውን ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች በሀገር ውስጥ ለመተካት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ስራዎችን በመሥራት ላይ መሆኑን አክለዋል። ከዩኒቨርሲቲው ተመራቂዎች መካከል ሀምሳ አለቃ ንጋቱ ሞላ እና ፍራኦል ጉተማ በተማሩት የሙያ መስክ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በቅንነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በቴክኖሎጂ ምርምር እና በጤናው ዘርፍ የሠራዊቱን አቅም ለማጎልበት እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡ አስር አለቃ ሃብታሙ ሊበን በበኩሉ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ገልጾ፥ እውቀቱን ለሌሎች የሰራዊቱ አባላት ለማካፈል ዝግጁ ነኝ ብሏል፡፡ በምርቃት መርኃ ግብሩ ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሽልማት ተበርክቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ
Jul 12, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቋል፡፡ ምክር ቤት ለሁለት ቀናት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤው የከተማ አስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት ሪፖርት፣ የ2018 በጀት ዓመት አቅጣጫ፣ የ2018 ረቂቅ በጀት እና የተለያዩ አዋጆች ላይ በመወያየት አጽድቋል። በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የቀረቡ የተለያዩ ተቋማት ሃላፊዎችን ሹመት አጽድቋል። በዚህም መሰረት አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ፣ አቶ መኮንን ያኢ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ፣ አቶ ኦሊያድ ስዩም የከተማ ቦታ ማስለቀቅ ጉዳዩች እና ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል። ምክር ቤቱ የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን የቀረበውን ረቂቅ የማሻሻያ አዋጅ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል። የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ውሳኔ፣ አስፈላጊነት፣ ዝርዝር ይዘት፣ ተሳትፎ፣ የሚያስገኘው ሃብት፣ የሚፈታው ችግር እንዲሁም ለከተማዋ ሁለንተናዊ እድገት ያለውን ተገቢነት ታሳቢ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። በዚህም መሠረት፦ - ከአዲስ አበባ የባህል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ተልዕኮዎች የቱሪዝም ዘርፉ ለብቻው የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ሆኖ ለከንቲባ ፅህፈት ቤት ተጠሪ በመሆን እንዲቋቋም፣ - የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ቢሮን ከትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ፅህፈት ቤት ጋር እንዲዋሃድ፣ - የአዲስ አበባ ማህበራዊ ትረስት ፈንድ ፅህፈት ቤት ከህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጋር እንዲዋሃድ እና - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አንድ ተግባር በከፊል ለውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ማስተላለፍ ላይ የቀረበውን ማሻሻያ አዋጅ ምክር ቤቱ በመሉ ድምፅ አፅድቋል።
የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ ሰራዊት ከመገንባት በተጓዳኝ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎችን እየፈጠረ ነው - ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ
Jul 12, 2025 118
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ ሰራዊት ከመገንባት በተጓዳኝ ዘመኑን የዋጁ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች እየፈጠረ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ ገለጹ። ዩኒቨርሲቲው በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ፣ በኃብት አስተዳደር እና በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ፤ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ወታደራዊ፣ ሲቪል እና የጎረቤት ሀገራት ተማሪዎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል ብለዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በእውቀትና በክህሎት ብቁ የሆነ የሰው ኃይል እያፈራ መሆኑንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የመከላከያ ሰራዊቱን የተልዕኮ አፈጻጸም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርሱ ወታደራዊና ሲቪል አመራሮችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገርን የሚያሻግሩ ሥራዎች በመስራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው የመከላከያን የሰለጠነ የሰራዊት ግንባታ በማገዝ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የሰራዊቱን ስምና ዝና በሚመጥን መልኩ የተዋቀረ ሲሆን ከመማር ማስተማር ስራዎች በተጓዳኝ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎችና ሌሎች ህብረተሰቡን የሚጠቅሙ ተግባራት እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሰራዊት ለመገንባት ከውጭ የምታስገባቸውን ቴክኖሎጂዎች በሀገር ውስጥ ለመተካት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ስራዎችን በመሥራት ላይ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ተመራቂዎች ባገኙት እውቀትና ከፍተኛ ክህሎት ሀገራቸውን በብቃት ማገልገል እንደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 152
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው በተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። አዋጁ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚቀርብ ማንኛውም ቅሬታ በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት የሚደነግግ ሲሆን የምርጫ ክልል አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ ይመደብ የነበረው ቀርቶ ቦርዱ አሰልጥኖ በሚመድባቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የሚያደርግ ነው። ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ አንድ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመመዝገብ የሚመለምለው አባል ከ5 ክልሎች የነበረ ሲሆን በተሻሻለው አዋጅ አንድ ፓርቲ አባላትን መመልመል ያለበት ከ7 ክልሎች ሊሆን እንደሚገባም በአዋጁ ተመላክቷል። አንድ ፓርቲ ከመንግሥት ድጋፍ ለማግኘት ከ30 በመቶ ከሚሆነው አባሉ የአባልነት መዋጮ መሰብሰብ እንደቅደመ ሁኔታም ተቀምጧል። በአዋጁ መሰረት ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ፓርቲዎች እስከ አምስት ዓመት ድረስ ሊታገዱ የሚችሉበት ድንጋጌም ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ከተሳተፉ መካከል የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ በምርጫ ጣቢያ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አይቶ ውሳኔ ይሰጣል የሚለው የአንቀጹ ክፍል ለአተገባበር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል ብለዋል። የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲዎች 30 በመቶ መዋጮ እንዲያሰባስቡ የተቀመጠው ድንጋጌ ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ወይ የሚለው ሊጤን እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው በአዋጁ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ድንጋጌዎች ሊካተቱ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሌ በሰጡት ማብራሪያ በአዋጁ ፓርቲዎች 30 በመቶ ያህል መዋጮ ከአባላት ሊሰበሰቡ እንደሚገባ የተደነገገው ፓርቲዎች በመንግሥት በጀት ላይ ብቻ እንዳይመሰረቱና ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። አዋጁ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን አካታች በሆነና ተሳትፏቸውን በሚያሳድግ መልኩ መቃኘቱን አንስተዋል። የመንግሥት ሰራተኞች በምርጫ ውድድር ወቅት ደሞዛቸውን ይዘው እንዲሳተፉ መደረጉ ለፖለቲካ ምህዳሩ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ በሰጡት ማብራሪያ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚነሱ ቅሬታዎች በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እንዲፈታ አቅጣጫ የተቀመጠው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታልሞ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲያም ሆኖ ቅሬታዬ አልተፈታም የሚል ማንኛውም አካል ጥያቄውን በየደረጃው የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ በበኩላቸው በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለአዋጁ ውሳኔ ሀሳብ የሚረዱ ግበዓቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር ላይ የፓርቲዎች ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በበኩላቸው ፓርቲዎች የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የበለጠ ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአባልነት መዋጮን በተመለከተም ፓርቲዎች አባላቶቻቸውን ሊያበረታቱ እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን ስራ ላይ ለማዋል የጀመራቸውን ተግባራት ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመው ፓርቲዎችም ይሄንኑ ስራ ሊደግፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት ይሰራል - አቶ ፍቃዱ ተሰማ
Jul 11, 2025 114
ጎንደር፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የተውጣጡ የፓርቲው የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች የተሳተፉበትና በጎንደር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የግምገማ መድረክ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ማምሻውን ተጠናቋል። አቶ ፍቃዱ ተሰማ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ፓርቲው መጪው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን መላ አባላቱን የማዘጋጀት ስራዎቹን በትኩረት ያከናውናል ብለዋል። ለዚህም የአባላት የስነ-ምግባር ደንቦችን በማዘጋጀት በምርጫው የትብብርና ፉክክር ዴሞክራሲያዊ ባህል እንዲዳብር እንደሚሰራም ተናግረዋል። አባላቱ በፓርቲው እሳቤዎች፣ መተዳደሪያ ደንብና አሰራሮች ዙሪያ ወጥና የተቀራረበ ግንዛቤ በመያዝ ተቋማዊ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ አቅማቸውን የመገንባት ስራ ይከናወናል ብለዋል። የፓርቲው አደረጃጀቶች በልማት በሠላምና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደፓርቲና መንግስት ሰፋ ያሉ ውጤቶች የተመዘገቡበትና የማንሰራራት ዘመን በተጨባጭ የታየበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዓመቱ በፓርቲው ውስጥ የአመለካከት፣ የተግባር አንድነትና ህብረ ብሔራዊነት የተጠናከረበት እንደነበርም ተናግረዋል። ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚደረገው ጥረት በጎ ጅምር የታየበት፣ ኢኮኖሚያዊ እድገቱ የሀገሪቱን በጀት በትሪሊዮን እንዲጸድቅ ያስቻለና የእዳ ቅነሳ የተደረገበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራና የከተሞች ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ እንደነበርም አብራርተዋል፡፡ በሠላም ማስከበር ሂደቱ የታጠቁ ኃይሎች የመንግስትን የሠላም አማራጭ ተቀብለው ተሃድሶ በመውሰድ በስፋት ወደ ሠላማዊ ህይወት መመለሳቸውንም አስታውሰዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳካ ፓርቲው የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ኃላፊው አረጋግጠዋል።
የከተማዋን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ተሳትፏቸውን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል
Jul 11, 2025 76
ወልዲያ ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፡- የወልዲያ ከተማን ሰላም አፅንቶ በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ተሳትፏቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ገለጹ። የከተማ አስተዳደሩ ከከተማው ወጣቶች ጋር በሰላምና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የምክክር መድረክ ዛሬ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ እንዳሉት፤ የአካባቢን ሠላም ለማፅናት ወጣቱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የድርሻውን ሲወጣ ቆይቷል። በዚህም የህግ የበላይነትን በማስከበር ሰላም ማስፈን መቻሉን ገልጸው፤ የተገኘውን ሰላም አስጠብቆ ዘላቂ ለማድረግ ወጣቶች ሲያበረክቱ የቆዩትን አስተዋጽኦ ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። በሰሜን ምስራቅ ዕዝ የ801ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌ በበኩላቸው፤ የመከላከያ ሰራዊቱ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላም ለማፅናት ውጤታማ ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። የወልዲያ ከተማ ወጣቶች ጽንፈኛውን አጥብቀው በመታገል ሲያበረክቱት የቆዩትን አስተዋጽኦ ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በውይይቱ የተሳተፉ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስከበር ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በምክክር መድረኩ ላይ ከከተማዋ የተወጣጡ ወጣቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ ይጀምራል
Jul 13, 2025 10
ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ እንደሚጀምር የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። ምክር ቤቱ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚያካሄደው ጉባኤ በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይም ተመልክቷል። የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ለኢዜአ እንዳሉት ምክር ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤውን ከነገ ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል። ምክር ቤቱ ከነገ ጀምሮ በሚያካሂደው 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውም በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ ተናግረዋል። ከአጀንዳዎቹ መካከልም የምክር ቤቱን የ8ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ የ2017 አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2018 ረቂቅ ዕቅድና በጀት ማፅደቅ እንደሚገኙበትም አፈ-ጉባኤዋ አመልክተዋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የኦዲት መስሪያ ቤቱ የ2017 ዓ/ም አፈጻጸም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድና በጀት ቀርቦ ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተገልጿል። እንዲሁም በምክር ቤቱ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና ሹመቶች ቀርበው እንደሚፀድቁም ዋና አፈ-ጉባኤዋ ተናግረዋል።
በክልሉ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Jul 13, 2025 28
አዳማ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት መከናወናቸውን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ አስታወቁ። የኦሮሚያ ክልል የ2017 በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ የስራ አፈፃፀም ግምገማ የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ፣ አፈጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማንን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአዳማ መካሄድ ጀምሯል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንደገለፁት በክልሉ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል። የክልሉ መንግሥት የአርሶና አርብቶ አደሩን እንዲሁም የከተማ ነዋሪዎችን ኑሮ ህይወት ለማሻሻልና ለመለወጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በስራ እድል ፈጠራ፣ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም በማዘመን፣ ገቢን በማሳደግና የአርብቶ አደሩን ህይወት መለወጥ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት መሰራቱን ጠቅሰዋል። መድረኩ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም በጥልቀት የሚፈተሽበትና ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው ለ2018 በጀት ዓመት አቅጣጫ የሚያዝበት መሆኑን አመላክተዋል። በየደረጃው ያለው አመራርም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተገኙ አበረታች ውጤቶችን በአዲሱ በጀት ዓመት በሙሉ አቅሙ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባው አስገንዝበዋል። "አዲሱ የበጀት ዓመት ለህዝቡ ቃል የገባንበት ሁለንተናዊ የልማት መስኮች ለማሳካት በሙሉ አቅማችን የምንረባረብበት ዓመት በመሆኑ በየደረጃው ያለው አመራር ራሱን ማዘጋጀት አለበት" ሲሉም አክለዋል። ለአገልግሎት አሰጣጥ እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ብልሹ አሰራሮች፣ ሌብነት፣ ህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ፣ የጎጠኝነትና የጥቅም ጥገኝነት አመለካከቶችና አስተሳሰቦችን ለማምከን መረባረብ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በበኩላቸው የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግሥትና በፓርቲ ስራ የተሻለ ተግባር የተከናወነበት ነው ብለዋል። በዚህም ጠንካራ የመንግስትና የፓርቲ አደረጃጀትና አሰራር ለመፍጠር አበረታች ስራዎች የተከናወኑበት መሆኑንም ተናግረዋል። የቀበሌ አደረጃጀትና መዋቅር በመዘርጋት በተለይም ህዝቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል። በዚህም በክልሉ የተሻለ ሰላም በማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ማከናወን የተቻለበት መሆኑን አመልክተዋል።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት በወታደራዊ ቴክኖሎጂ ፈጠራ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ነው - ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር)
Jul 12, 2025 160
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በወታደራዊ ቴክኖሎጂ ፈጠራ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ እንደሚገኝ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ እና በኃብት አስተዳደር እንዲሁም በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። መንግሥት ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታ እንዲሁም ወታደራዊ ቴክኖሎጂ ማፍለቅና ማምረት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በእውቀት፣ በዓላማ እና በሙያዊ ክህሎት የታነጹ ጀግና የሰራዊት አባላት እና ቴክኖሎጂ ፈጣሪዎችን እያፈራን ነው ብለዋል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት በወታደራዊ ቴክኖሎጂ ፈጠራ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲም የሰለጠነ የሠራዊት አባላትንና ሲቪል አመራር በማፍራት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። የሠራዊቱን የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ብቃት ለማላቅ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይም ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ ማገዝ የሚችሉ ብቁና ሥነ-ምግባር ያላቸውን ሙያተኞች እያፈራ መሆኑን ጠቁመዋል። ዩኒቨርሲቲው ለሀገርና ለመጪው ትውልድ የሚሻገር ስራ መሥራቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸው፥ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎትን በማስፋት እንዲተገብርም ተናግረዋል። በዘመናዊ የሠራዊት ግንባታ ሂደት እውቀትና ቴክኖሎጂ መሠረታዊ መሆኑን አንስተው ለዚህም ዩኒቨርሲቲው ከዚህ አኳያ አመርቂ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተመራቂዎች በታማኝነት፣ በቅንነትና በስነምግባር ሀገራቸውን ማገልገል እንዳለባቸውም አፅንኦት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ፤ ዩኒቨርሲቲው በእውቀትና በክህሎት ብቁ የሆነ የሰው ኃይል እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የመከላከያ ሰራዊቱን የተልዕኮ አፈጻጸም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ወታደራዊና ሲቪል አመራሮችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገርን የሚያሻግሩ ሥራዎች በመስራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው የመከላከያን የሰለጠነ የሰራዊት ግንባታ በማገዝ ላይ መሆኑንም አንስተዋል። ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባቸውን ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች በሀገር ውስጥ ለመተካት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ስራዎችን በመሥራት ላይ መሆኑን አክለዋል። ከዩኒቨርሲቲው ተመራቂዎች መካከል ሀምሳ አለቃ ንጋቱ ሞላ እና ፍራኦል ጉተማ በተማሩት የሙያ መስክ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በቅንነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በቴክኖሎጂ ምርምር እና በጤናው ዘርፍ የሠራዊቱን አቅም ለማጎልበት እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡ አስር አለቃ ሃብታሙ ሊበን በበኩሉ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ገልጾ፥ እውቀቱን ለሌሎች የሰራዊቱ አባላት ለማካፈል ዝግጁ ነኝ ብሏል፡፡ በምርቃት መርኃ ግብሩ ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሽልማት ተበርክቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ
Jul 12, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቋል፡፡ ምክር ቤት ለሁለት ቀናት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤው የከተማ አስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት ሪፖርት፣ የ2018 በጀት ዓመት አቅጣጫ፣ የ2018 ረቂቅ በጀት እና የተለያዩ አዋጆች ላይ በመወያየት አጽድቋል። በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የቀረቡ የተለያዩ ተቋማት ሃላፊዎችን ሹመት አጽድቋል። በዚህም መሰረት አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ፣ አቶ መኮንን ያኢ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ፣ አቶ ኦሊያድ ስዩም የከተማ ቦታ ማስለቀቅ ጉዳዩች እና ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል። ምክር ቤቱ የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን የቀረበውን ረቂቅ የማሻሻያ አዋጅ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል። የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ውሳኔ፣ አስፈላጊነት፣ ዝርዝር ይዘት፣ ተሳትፎ፣ የሚያስገኘው ሃብት፣ የሚፈታው ችግር እንዲሁም ለከተማዋ ሁለንተናዊ እድገት ያለውን ተገቢነት ታሳቢ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። በዚህም መሠረት፦ - ከአዲስ አበባ የባህል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ተልዕኮዎች የቱሪዝም ዘርፉ ለብቻው የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ሆኖ ለከንቲባ ፅህፈት ቤት ተጠሪ በመሆን እንዲቋቋም፣ - የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ቢሮን ከትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ፅህፈት ቤት ጋር እንዲዋሃድ፣ - የአዲስ አበባ ማህበራዊ ትረስት ፈንድ ፅህፈት ቤት ከህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጋር እንዲዋሃድ እና - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አንድ ተግባር በከፊል ለውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ማስተላለፍ ላይ የቀረበውን ማሻሻያ አዋጅ ምክር ቤቱ በመሉ ድምፅ አፅድቋል።
የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ ሰራዊት ከመገንባት በተጓዳኝ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎችን እየፈጠረ ነው - ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ
Jul 12, 2025 118
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ ሰራዊት ከመገንባት በተጓዳኝ ዘመኑን የዋጁ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች እየፈጠረ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ ገለጹ። ዩኒቨርሲቲው በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ፣ በኃብት አስተዳደር እና በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ፤ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ወታደራዊ፣ ሲቪል እና የጎረቤት ሀገራት ተማሪዎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል ብለዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በእውቀትና በክህሎት ብቁ የሆነ የሰው ኃይል እያፈራ መሆኑንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የመከላከያ ሰራዊቱን የተልዕኮ አፈጻጸም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርሱ ወታደራዊና ሲቪል አመራሮችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገርን የሚያሻግሩ ሥራዎች በመስራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው የመከላከያን የሰለጠነ የሰራዊት ግንባታ በማገዝ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የሰራዊቱን ስምና ዝና በሚመጥን መልኩ የተዋቀረ ሲሆን ከመማር ማስተማር ስራዎች በተጓዳኝ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎችና ሌሎች ህብረተሰቡን የሚጠቅሙ ተግባራት እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሰራዊት ለመገንባት ከውጭ የምታስገባቸውን ቴክኖሎጂዎች በሀገር ውስጥ ለመተካት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ስራዎችን በመሥራት ላይ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ተመራቂዎች ባገኙት እውቀትና ከፍተኛ ክህሎት ሀገራቸውን በብቃት ማገልገል እንደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 152
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው በተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። አዋጁ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚቀርብ ማንኛውም ቅሬታ በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት የሚደነግግ ሲሆን የምርጫ ክልል አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ ይመደብ የነበረው ቀርቶ ቦርዱ አሰልጥኖ በሚመድባቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የሚያደርግ ነው። ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ አንድ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመመዝገብ የሚመለምለው አባል ከ5 ክልሎች የነበረ ሲሆን በተሻሻለው አዋጅ አንድ ፓርቲ አባላትን መመልመል ያለበት ከ7 ክልሎች ሊሆን እንደሚገባም በአዋጁ ተመላክቷል። አንድ ፓርቲ ከመንግሥት ድጋፍ ለማግኘት ከ30 በመቶ ከሚሆነው አባሉ የአባልነት መዋጮ መሰብሰብ እንደቅደመ ሁኔታም ተቀምጧል። በአዋጁ መሰረት ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ፓርቲዎች እስከ አምስት ዓመት ድረስ ሊታገዱ የሚችሉበት ድንጋጌም ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ከተሳተፉ መካከል የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ በምርጫ ጣቢያ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አይቶ ውሳኔ ይሰጣል የሚለው የአንቀጹ ክፍል ለአተገባበር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል ብለዋል። የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲዎች 30 በመቶ መዋጮ እንዲያሰባስቡ የተቀመጠው ድንጋጌ ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ወይ የሚለው ሊጤን እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው በአዋጁ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ድንጋጌዎች ሊካተቱ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሌ በሰጡት ማብራሪያ በአዋጁ ፓርቲዎች 30 በመቶ ያህል መዋጮ ከአባላት ሊሰበሰቡ እንደሚገባ የተደነገገው ፓርቲዎች በመንግሥት በጀት ላይ ብቻ እንዳይመሰረቱና ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። አዋጁ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን አካታች በሆነና ተሳትፏቸውን በሚያሳድግ መልኩ መቃኘቱን አንስተዋል። የመንግሥት ሰራተኞች በምርጫ ውድድር ወቅት ደሞዛቸውን ይዘው እንዲሳተፉ መደረጉ ለፖለቲካ ምህዳሩ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ በሰጡት ማብራሪያ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚነሱ ቅሬታዎች በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እንዲፈታ አቅጣጫ የተቀመጠው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታልሞ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲያም ሆኖ ቅሬታዬ አልተፈታም የሚል ማንኛውም አካል ጥያቄውን በየደረጃው የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ በበኩላቸው በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለአዋጁ ውሳኔ ሀሳብ የሚረዱ ግበዓቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር ላይ የፓርቲዎች ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በበኩላቸው ፓርቲዎች የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የበለጠ ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአባልነት መዋጮን በተመለከተም ፓርቲዎች አባላቶቻቸውን ሊያበረታቱ እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን ስራ ላይ ለማዋል የጀመራቸውን ተግባራት ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመው ፓርቲዎችም ይሄንኑ ስራ ሊደግፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት ይሰራል - አቶ ፍቃዱ ተሰማ
Jul 11, 2025 114
ጎንደር፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የተውጣጡ የፓርቲው የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች የተሳተፉበትና በጎንደር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የግምገማ መድረክ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ማምሻውን ተጠናቋል። አቶ ፍቃዱ ተሰማ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ፓርቲው መጪው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን መላ አባላቱን የማዘጋጀት ስራዎቹን በትኩረት ያከናውናል ብለዋል። ለዚህም የአባላት የስነ-ምግባር ደንቦችን በማዘጋጀት በምርጫው የትብብርና ፉክክር ዴሞክራሲያዊ ባህል እንዲዳብር እንደሚሰራም ተናግረዋል። አባላቱ በፓርቲው እሳቤዎች፣ መተዳደሪያ ደንብና አሰራሮች ዙሪያ ወጥና የተቀራረበ ግንዛቤ በመያዝ ተቋማዊ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ አቅማቸውን የመገንባት ስራ ይከናወናል ብለዋል። የፓርቲው አደረጃጀቶች በልማት በሠላምና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደፓርቲና መንግስት ሰፋ ያሉ ውጤቶች የተመዘገቡበትና የማንሰራራት ዘመን በተጨባጭ የታየበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዓመቱ በፓርቲው ውስጥ የአመለካከት፣ የተግባር አንድነትና ህብረ ብሔራዊነት የተጠናከረበት እንደነበርም ተናግረዋል። ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚደረገው ጥረት በጎ ጅምር የታየበት፣ ኢኮኖሚያዊ እድገቱ የሀገሪቱን በጀት በትሪሊዮን እንዲጸድቅ ያስቻለና የእዳ ቅነሳ የተደረገበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራና የከተሞች ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ እንደነበርም አብራርተዋል፡፡ በሠላም ማስከበር ሂደቱ የታጠቁ ኃይሎች የመንግስትን የሠላም አማራጭ ተቀብለው ተሃድሶ በመውሰድ በስፋት ወደ ሠላማዊ ህይወት መመለሳቸውንም አስታውሰዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳካ ፓርቲው የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ኃላፊው አረጋግጠዋል።
የከተማዋን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ተሳትፏቸውን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል
Jul 11, 2025 76
ወልዲያ ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፡- የወልዲያ ከተማን ሰላም አፅንቶ በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ተሳትፏቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ገለጹ። የከተማ አስተዳደሩ ከከተማው ወጣቶች ጋር በሰላምና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የምክክር መድረክ ዛሬ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ እንዳሉት፤ የአካባቢን ሠላም ለማፅናት ወጣቱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የድርሻውን ሲወጣ ቆይቷል። በዚህም የህግ የበላይነትን በማስከበር ሰላም ማስፈን መቻሉን ገልጸው፤ የተገኘውን ሰላም አስጠብቆ ዘላቂ ለማድረግ ወጣቶች ሲያበረክቱ የቆዩትን አስተዋጽኦ ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። በሰሜን ምስራቅ ዕዝ የ801ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌ በበኩላቸው፤ የመከላከያ ሰራዊቱ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላም ለማፅናት ውጤታማ ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። የወልዲያ ከተማ ወጣቶች ጽንፈኛውን አጥብቀው በመታገል ሲያበረክቱት የቆዩትን አስተዋጽኦ ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በውይይቱ የተሳተፉ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስከበር ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በምክክር መድረኩ ላይ ከከተማዋ የተወጣጡ ወጣቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ማህበራዊ
አሰባሳቢ ትርክትን በሚያሰርጹ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር ሚናችንን እናጎለብታለን- ወጣቶች
Jul 13, 2025 37
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ አሰባሳቢ ትርክትን በሚያሰርጹ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር የሚጠበቅብንን ድርሻ ይበልጥ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር አባላት ተናገሩ። አሰባሳቢ ትርክትን በመገንባት ሂደት ወጣቶች እያበረከቱት ያለውን አስተዋጽኦ በተመለከተ ኢዜአ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር አባላትን አነጋግሯል። ወጣት አቤል ኃይሉ በሰጠው አስተያየት እንደገለጸው፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት መንግስት የወጣቱን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራትን በስፋት አከናውኗል። በተለይም በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ የወጣቱ ተሳትፎ እንዲጎለብት በማድረግ አካታች የስራ ፈጠራና እድል ተጠቃሚነት፣ በሰላም ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ፣ በግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ወጣቱን ያማከለ ስራ መከናወኑን ገልጿል። ይህም ወጣቱ የማህበረሰብ ክፍል በአገሩ የትኛውም ጉዳይ ላይ በባለቤትነትና በሃላፊነት እንዲሳተፍ የሚያነሳሳ ከመሆኑም ባሻገር በአገር ሁለንተናዊ ልማት ላይ አስተዋጽኦ እንዲኖረው ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ነው ያለው። የዚህ ዘመን ትውልድ የራሱን አሻራ ከሚያኖርበት ተግባራት አንዱ የጋራ አሰባሳቢ ትርክትን ማስረጽ መሆኑን ጠቅሶ፤ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያውያንን በጋራ ሊያሰባስቡ የሚችሉ በርካታ ተግባራት መኖራቸውን አብራርቷል። በመሆኑም አሰባሳቢ ትርክትን በሚያሰርጹ ተግባራት ላይ በመሳተፍ የአገረ መንግስት ግንባታው ሂደት አካል ለመሆን የሚጠበቅበትን ሃላፊነት እየተወጣ መሆኑን ተናግሯል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት መልካም በንቲ በበኩሏ እንደገለጸችው፤ ወጣቱ ጊዜውን በአግባቡ ጥቅም ላይ በማዋል ከራሱ አልፎ አገሩን የሚያገለግልበትን እድል በማመቻቸት ረገድ መንግስት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን አከናውኗል። ለአብነትም የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ወጣቱ ማህበረሰቡንና አገሩን በቅንነት እንዲያገለግልና ለመልካም ተግባር በጋራ እንዲሰባሰብ እድል ፈጥሯል ነው ያለችው። ይህም አገሩን የሚወድ ፣ለማህበረሰቡና ለአገሩ ተቆርቋሪና መልካም ስነ-ምግባር ያለው ትውልድ እንዲፈጠር በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ወጣቱ ትውልድ አገርን እየሰራ ለቀጣዩ ትውልድ ማሻገር የሚጠበቅበት መሆኑን በመጠቆም፤ አሰባሳቢ ትርክትን ማስረጽና በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቅበታል ብላለች። በመሆኑም እንደ አገር የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ወደ እድል በመቀየር ወጣቱ ለአገረ መንግስት ግንባታው ኃላፊነቱን መወጣት አለበት ነው ያለችው። ወጣት መሰረት ሙልዬ እንዲሁ ወጣቱ በአሰባሳቢ ትርክት ዙሪያ ያለው አዎንታዊ አመለካከት እየዳበረ መምጣቱን ገልጻለች። ይህም አብሮነትን የሚያጎለብትና የዜጎችን የእርስ በእርስ ግንኙነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጻ፤ ወጣቱ የገዢ ትርክት እሳቤዎችን መገንዘብና ማስፋት ይጠበቅበታል ብላለች።
በሲዳማ ክልል የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር እርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህል እንዲጎለብት አግዟል - ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Jul 12, 2025 83
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር የህብረተሰቡን እርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህል እንዲጎለብት ማገዙን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ዳዬ ከተማ አስጀምረዋል። አቶ ደስታ አገልግሎቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በህብረተሰቡ ውስጥ የመደጋገፍ ባህል እንዲጎለብት አግዟል። በአገልግሎቱ ወጣቶች፣ የመንግስት ተቋማት፣ ሠራተኞች፣ ባለሀብቶችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውንና በልማት ስራውም በርካታ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። ለአብነትም ባለፈው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ3ሺህ በላይ ቤቶችን በማደስና በአዲስ መልክ መገንባት ለብዙዎች እፎይታ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መኖሪያ ቤታቸው የሚገነባላቸው አቅመ ደካሞች ኑሯቸውን በዘላቂነት ለማሻሻል ቋሚ የገቢ ማስገኛ ሥራ ይፈጠርላቸዋል ብለዋል። የክልሉ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ እመቤት ኢሳያስ በበኩላቸው በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በርካታ ወጣቶችን በማሳተፍ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ነው ያሉት። በአገልግሎቱ 800ሺህ ወጣቶችን በማሳተፍ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤት መልሶ መገንባት፣ ደም መለገስ፣ ማዕድ ማጋራት፣ ትምህርትና ችግኝ ተከላን ጨምሮ በ14 መስኮች ወጣቶችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ ብለዋል። ከተሳታፊ ወጣቶች መካከል የዳዬ ከተማ ነዋሪ ወጣት ለማ ለገሰ በየዓመቱ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በንቃት መሳተፉ ውስጣዊ እርካታን እንደሚሰጠው ተናግሯል። በተለይ በሰብአዊ የድጋፍ ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የአቅመ ደካሞችን ማህበራዊ ችግር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረጉ ደስተኛ መሆኑን ገልጿል። ቤታቸው በአዲስ መልክ ግንባታ ከተጀመረላቸው ነዋሪዎች መካከል ከአራት ልጆቻቸው ጋር የሚኖሩት ወይዘሮ እታፈራሁ እርገጤ በበጎ ፈቃደኞች በአዲስ መልክ የቤታቸው ግንባታ በመጀመሩ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ በየነ በራሳ፣ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት የተገኙ ሲሆን የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሀግብርም ተከናውኗል።
ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው የጤና ተቋማት ማጠናከር ስራ ላይ በመሳተፍ ድጋፍ እያደረገ ነው
Jul 12, 2025 64
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 5/2017 (ኢዜአ):- ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በአካባቢው የሚገኙ የጤና ተቋማት ማጠናከር ስራ ላይ በመሳተፍ ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ ። ዩኒቨርሲቲው በሀድያ ዞን በሆመቾ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባውን ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት አስመርቆ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዳዊት ሀየሶ (ዶ/ር) እንዳሉት ፤ ተቋሙ ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ ነው። በአካባቢው የሚገኙ የጤና ተቋማት ያሉባቸውን የህክምና ግብዓትና ሌሎች ቁሳቁሶችን አሟልተው የተሻለ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጡ እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከ12 ሚሊየን ብር በላይ በጀት በመመደብ በአካባቢው የሚገኙ 4 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎችን የመድኃኒት አቅርቦት ችግር ለማቃለል የማህበረሰብ መድሀኒት ቤቶችን በመገንባት የማስረከብ ስራ እያከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡ የሀድያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ተወካይ የሆኑት አቶ ሚሻሞ ወርቅነህ በበኩላቸው፤ በዞኑ የሚገኙ የህክምና ተቋማት ያለባቸውን የመድኃኒት አቅርቦት ችግር ለማቃለል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተገንብቶ ዛሬ ለአገልግሎት የበቃው የማህበረሰብ መድሀኒት ቤት የዚህ ጥረት አካል እንደሆነ ጠቅሰዋል። የሆመቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ምስጋና አለሙ ፤ ዛሬ ለአገልገሎት የበቃው የማህበረሰብ መድሃኒት ቤቱ በሆስፒታሉ የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያግዝ ነው የገለጹት፡፡ በመርሐ ግብሩ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የችግኝ ተከላ ያከናወኑ ሲሆን፤ በዚህም የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ወጣቶች ለወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስኬታማነት የድርሻቸውን ይወጣሉ
Jul 12, 2025 45
ድሬዳዋ፣ ሐምሌ 5/2017 (ኢዜአ)፡- ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አንድነትንና መተጋገዝን ስለሚያጎለብት ለስኬታማነቱ የድርሻቸውን እንደሚወጡ በድሬዳዋ በአገልግሎቱ እየተሳተፉ ያሉ ወጣቶች ገለጹ። በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስተባባሪነት የሚመራው የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተሳታፊዎች ዛሬ በድሬዳዋ የጽዳት ዘመቻ አካሂደዋል። በአገልግሎቱ የተሳተፉ ወጣቶች ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በመሳተፍ የዜጎችን ማህበራዊ ችግሮች ለማቃለል እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ተሳታፊዎች መካከል ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመጣችው ወጣት ሃና፤ ለበጎ ተግባር ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ ወጣቶች መሰባሰባቸውን ገልጻ ይህም የባህል ትውውቅ ለማድረግና አንድነትን ለማጠናከር እንደሚያግዛቸው ተናግራለች። በድሬዳዋ በሚኖራት ቆይታም በጽዳት ሥራ፣ በችግኝ ተከላና በደም ልገሳ መርሀግብሮች በመሳተፍ የበኩሏን ለመወጣት መዘጋጀቷን ተናግራለች። ህዝብን ባሳተፈ መንገድ ሀገርን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የድርሻውን ለመወጣት በበጎ ፍቃድ አገልግሎት መሳተፉን የገለጸው ደግሞ የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪ ወጣት ባጫ ነመራ ነው። ለበጎ ፈቃድ ሥራው ወደ ተለያዩ ክልሎች በተጓዘበት ወቅት ያየው ብዝሀ ወግና ባህል ኢትዮጵያን በተሻለ ለማወቅ እንዳስቻለውም ተናግሯል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የወጣቶች ተሳትፎና አደረጃጀት አቅም ግንባታ ዴስክ ኃላፊ አቶ አድነው አበራ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መርህ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለአራተኛ ጊዜ በመላው ኢትዮጵያ እየተካሄደ ይገኛል። ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እያቃለለ ከመምጣቱ ባሻገር የባህል ትውውቅን እያጎለበተ መሆኑንም ተናግረዋል። የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ትውልዱ በቅብብሎሽና በመተጋገዝ የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርለት ገልጸው፣ በልማት ስራውም አዲሱ ትውልድ ሀላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ካሊድ መሐመድ በበኩላቸው፣ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች ድሬዳዋ ተገኝተው ላበረከቱት አርአያነት ያለው ተግባር አመስግነዋል። በመረሀ ግብሩም በ14 የልማት መስኮች በገጠርና በከተማ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።
ኢኮኖሚ
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ወጪን በራስ አቅም የመሸፈን ሂደቱን አሳድጓል
Jul 13, 2025 13
አሶሳ፤ ሐምሌ 6/2017 (ኢዜአ)፦በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017 በጀት ዓመት በቅንጅት በተሰበሰበ ገቢ ወጪን በራስ የመሸፈን ሂደቱን በማሳደግ ላይ መሆኑን የክልሉ ገቢዎች ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ተፈሪ አበበ ለኢዜአ እንዳስታወቁት፤ በበጀት ዓመቱ 4 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዞ ሲሰራ ቆይቷል። በበጀት ዓመቱን በተቀናጀ አኳኋን በተሰራው ሥራም ከእቅድ በላይ አምስት ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ተችሏል ብለዋል። ከተለያዩ ተቋማት ጋር የነበረው ቅንጅታዊ አሰራር መጠናከር፣ ዘመናዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓት መስፈን እና የህግ አሰራሮች ላይ ማሻሻያ መደረጉ የላቀ አፈጻጸም እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል። ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ46 በመቶ ብልጫ እንዳለው አቶ ተፈሪ አስታውቀዋል። ክልሉ የራሱን ወጪ የመሸፈን አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ዓመት የራሱን ወጪ የመሸፈን አቅሙ ወደ 60 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። ግብር ከፋዩ ግብርን በወቅቱ የመክፈል እና የግብርን አስፈላጊነት እየተገነዘበ በመሆኑ የታክስ ማጭበርበር እና ስወራ እየቀነሰ መምጣቱን አመላክተዋል። ክልሉ ካለው የገቢ አማራጭ አንፃር መሰብሰብ የሚገባውን ገቢ አላገኘም ያሉት አቶ ተፈሪ ተጨማሪ የገቢ አማራጮች ላይ ጥናት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በዘንድሮ የመኸር ወቅት እስከ አሁን 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል
Jul 13, 2025 30
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦በ2017/18 የመኸር ወቅት እስከ አሁን 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ። የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተከናወነ ይገኛል። በግብርናው ዘርፍ በመኸር፣ በበልግ እንዲሁም በመስኖ ልማት ስራዎች ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች አመርቂ ውጤቶች መመዝገቡን አስታውሰዋል። በዚህ ዓመት በመላ አገሪቱ 21 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመኸር እርሻ በተለያዩ ሰብሎች ዘር እንደሚሸፈን ገልጸዋል። አሁን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የዘር ስራ የሚከናወንበት በመሆኑ እንደ በቆሎ ያሉ የአገዳ ሰብሎች ቀድሞ መዘራታቸውን ጠቁመው፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስና ሌሎች እንደየ አካባቢው ሥነ-ምህዳር እየተዘሩ መሆኑን ተናግረዋል። ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም እና ለአርሶ አደሩ ግንዛቤ በመፍጠር ጭምር በመሰራቱ በዚህ ዓመት የተሻለ ምርት ይጠበቃል ብለዋል። ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሚያችሉ የአፈር ማዳበሪያ፣ የምርጥ ዘር እና የተለያዩ ግብዓቶች ለአርሶ አደሩ በወቅቱ እንዲደርሱ መደረጉንም ተናግረዋል። የመኸር የእርሻ ጊዜ ለኢትዮጵያ ትልቁ የምርት ጊዜ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ በዓመቱ በአጠቃላይ ከሚመረተው ምርት 70 በመቶ የሚሆነው በዚሁ ወቅት የሚለማ መሆኑንም ተናግረዋል። ሚኒስትሩ እንደገለጹት ዘንድሮ 13 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም የሚለማ ሲሆን ይህም ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር እድገት ማሳየቱን ገልጸዋል። አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም በሚሰራበት ወቅት ምርታማነቱ የበለጠ እንደሚጨምር አስታውሰው ይህም የበለጠ መጠናከር እንዳለበት አስታውቀዋል። 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት በመካናይዜሽን የታረሰ መሆኑን ገልጸው ይህም ከባለፈው በ1 ሚሊየን ሄክታር መሬት ብልጫ እንዳለው ጠቅሰዋል። የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመንና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትልቁ ለውጥ የአርሶ አደሮች የቴክኖሎጂን መጠቀም ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ መሆኑንም ተናግረዋል። በመኸር ወቅት 21 ሚሊየን ሄክታር መሬት በሰብል በመሸፈን ከ659 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል።
የገጠር ኮሪደር ልማት የኅብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ኢኒሼቲቭ ነው
Jul 12, 2025 68
ሚዛን አማን፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የገጠር ኮሪደር ልማት የኅብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና ሴክተር ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ ገለጹ። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና ተጠሪ ተቋማት በቤንች ሸኮ ዞን የገጠር ኮሪደር ልማትን እሳቤ አሟልተው የሚገነቡ አምስት ሞዴል ቤቶች ግንባታ ሥራን አስጀምረዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና ሴክተር ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ እንዳሉት የገጠር ኮሪደር ልማት እሳቤ የገጠር ነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ሀገራዊ ኢኒሼቲቭ ነው። በዚህም ለአርሶ እና አርብቶ አደሩ ጤናማና ምቹ የአኗኗር ስርአት ከመፍጠር ባለፈ ከምርታማነት ጋር ለማስተሳሰር ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የሞዴል ቤቶች ግንባታ ጽዳቱን የጠበቀ መኖሪያ ቤት ከመገንባት ጀምሮ የሌማት ትሩፋት፣ የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የአረንጓዴ ሥፍራና ለማኅበራዊ አገልግሎት የሚውሉ መስኮችን ያካተተ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የገጠር ኮሪደር እሳቤን ታሳቢ ያደረጉ አምስት ሞዴል ቤቶችን በጉራፈርዳ ወረዳ እንደሚገነባና ከእዚህም ሌሎች አይተው እንዲያስፋፉ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት ተግባር የገጠር ነዋሪዎች አኗኗርን ዘመናዊ በማድረግ ለብልጽግና ጉዞ ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑንም ነው ሚኒስትር ዴኤታው የተናገሩት። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የከተማና የገጠር ነዋሪዎችን ያማከለ የልማት ኢኒሼቲቮችን በመዘርጋት ሁሉንም ተጠቃሚ ለማድረግ እየሠራ ነው ብለዋል። በክልሉ የተለያዩ ቀበሌዎች የተጀመሩ የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸው፣ ልማቱንም በምግብ ራስን ለመቻል ከሚሰራው ሥራ ጋር ማቆራኘት እንደሚገባ ገልጸዋል።
በድሬዳዋ አስተዳደር የሚሰበሰብ ገቢ መጨመር የህዝብን የልማት ጥያቄ በራስ ገቢ የመመለስ አቅምን አሳድጎታል
Jul 12, 2025 63
ድሬዳዋ፣ ሐምሌ 5/2017 (ኢዜአ)፡-በድሬዳዋ አስተዳደር የሚሰበሰበው ገቢ እየጨመረ መምጣት የህዝብን የልማት ጥያቄ በራስ ገቢ የመመለስ አቅምን ከ70 በመቶ በላይ ማድረሱን የአስተዳደሩ ገቢዎች ባለስልጣን አስታወቀ። የድሬዳዋ ገቢዎች ባለስልጣን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡም ተገልጿል። የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልሰላም መሐመድ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ዳይሬክተሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በድሬዳዋ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ሃብት የሚስተካከል ገቢ ለመሰብሰብ በተሰራው ሥራ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በአስተዳደሩ የነበረውን ዓመታዊ ገቢ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር እንደነበር አስታውሰው፣ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ መሰረታዊ ሪፎርም በመካሄዱና ዲጂታል አሠራሮች በመዘርጋታቸው ገቢው በየዓመቱ በቢሊዮን ብሮች ጨምሯል ብለዋል። ለአብነት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከመንግስትና ከማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች 6 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ተችሏል ብለዋል። በእዚህም የዕቅዱን 86 በመቶ ማሳካት መቻሉን ጠቅሰው የዘንድሮ ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል። በአስተዳደሩ የሚሰበሰበው ገቢ እየጨመረ መምጣት የህዝብን የልማት ጥያቄዎች በራስ ገቢ የመመለስ አቅምን በማሳደግ ከ70 በመቶ በላይ ማድረሱንም አቶ አብዱልሰላም አስታውቀዋል። ይህም ቢሆን እያደገ የመጣውን የነዋሪውን የልማት ጥያቄዎች በአግባቡ ለመመለስ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራ በቀጣይም ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚከናወን አቶ አብዱልሰላም ገልጸዋል። በቀጣይም በተለይ በዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሠራሮችን በማረም፣ ዘመናዊ የግብር አሰባሰብ ስርአትን በመተግበርና ያለ ደረሰኝ የሚፈፀም ግብይትን በመከላከል የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ይሰራል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከ19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች ተመዝግበዋል
Jul 13, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እስካሁን ከ19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች መመዝገባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ገለጹ። በኢትዮጵያ የነዋሪዎችን የመታወቅ መብት ለማረጋገጥ፣ በአገልግሎት ሰጭና ተቀባዮች መካከል መተማመን እንዲዳብር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና የተሳለጠ አሰራር ለመዘርጋት የዲጂታል መታወቂያ ገቢራዊ ተደርጓል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት በአዲስ አበባ እና በክልል የዲጂታል የመታወቂያ ምዝገባ ማከናወንና ከተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ፡፡ ይህንን ተከትሎ እስካሁን 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን ነዋሪዎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውንና ከ55 ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል ፡፡ በ2018 በጀት አመት የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን የበለጠ ለማሳደግ እቅድ መያዙንና ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡ በተለይ በክልሎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን ይበልጥ ለማስፋት ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት አመት በክልሎች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መሰራቱን እና በዚህም ውጤት መገኘቱንም አስታውቀዋል። ለዚህ ከከፍተኛ አመራሩ ጀምሮ ለስራው ትኩረት ሰጥቶ ህብረተሰቡ የዲጂታል መታወቂያ እንዲመዘገብ በማድረግ በኩል ትልቅ ተግባር ተከናውኗል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ትምህርት ማህበረሰቡ የፋይዳ ዲጂታል ትግበራ በትምህርት ቤቶች ውጤታማ እንዲሆን ያከናወነውን ተግባር በተሞክሮነት ወደ ክልሎች የማስፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለጻ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት የዲጂታል አገልግሎቱን ለማሳለጥና ጠንካራ የሆነ የማንነት አስተዳደር ስርዓት ለመፍጠር እያገዘ ይገኛል፡፡
በክረምት በተከታተልነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስልጠና የቀሰምነው ዕውቀት በትምህርት ቤት ውጤታማ እንድንሆን አግዞናል
Jul 12, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የታዳጊዎች የክረምት ስልጠና የቀሰሙት ዕውቀት በትምህርት ቤት ውጤታማ እንዲሆኑ እንዳገዛቸው ቀደም ሲል የሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤ አይ) ስልጠና የተከታተሉ ታዳጊዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በተለያዩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች አራተኛውን የታዳጊዎች የክረምት ስልጠና በሳይንስ ሙዚየም አስጀምሯል። ስልጠናውን ተከታትለው የጨረሱ ታዳጊዎች ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ ቀደም ሲል የወሰዱት ስልጠና ህልማቸውን እውን ለማድረግ በሚሰሩት ስራ በብዙ መንገድ ደግፏቸዋል። በትምህርት ማዘመን የሚያስችል ፕሮጀክት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ወጣት ሰለሞን መብሬ የ2014 የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስልጠና ወስዶ አጠናቋል። እንደወጣት ሰለሞን ገለጻ፤ አሰልጣኞቹ በዘርፉ ያላቸው እውቀት ከፍተኛ በመሆኑ ፈጠራን ለመውደድና ለማሰብ አስችሏቸዋል። በዚህም የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ወደ ጥቅም መቀየር የሚያስችል አቅም ማዳበራቸውን ጠቁሞ፤ በተለይ በቡድን የመስራት መንፈስ እንዲላበሱ እንደረዳቸው ተናግሯል። የ12ኛ ክፍል ተማሪ ዲቦራ ወንድወሰን የ2015 የሰው ሰራሽ አስተውሎት የክረምት ስልጠና ተመራቂ ነች። በተከታተለቸው ስልጠና በአጭር ጊዜ ውስጥ አዳዲስ ነገሮች ለመገንዘብ መቻልዋን ተናግራለች። እንዲሁም በቡድን የመስራት ችሎታና ችግሮችን የመፍታት አቅም ለማዳበር እንደረዳትም ነው የገለፀችው። አስተያየት ሰጪዎቹ ስልጠናው የሀገር ብሎም የማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚያስችሉ መርሃ ግብሮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተናግረዋል። በዚህም የአራተኛውን ዙር የሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤአይ) የክረምት ስልጠና የሚወስዱ ታዳጊ ተማሪዎች ያገኙትን እድል በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል። በሌላ በኩል ዘንድሮ ወደ ስልጠናው የሚገቡ ሰልጣኞች በበኩላቸው፤ በስልጠናው የተሻለ እውቀትና ችሎታ አዳብረው ለመውጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ተማሪ ቅዱስ ሙሴ የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤአይ) መማር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን በማመን ወደ ስልጠናው መምጣቱን ተናግሯል። ታዳጊዎች እንደዚህ ዓይነት ስልጠናዎች መሳተፋቸው ትልቅ ህልም እንዲያልሙ ና ህልማቸውን በተጨባጭ በመተርጎም ከራሳቸው አልፈው ለሀገር እንዲተርፉ ይረዳል ብሏል። የስምንተኛ ክፍል ተማሪ ኑሃሚን ጥበቡ እንደምትናገረው፤ አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ ስራዎችን ቀለል ባለ መልኩ ለማከናወን የሚረዳ በመሆኑ ሥልጠናውን ለመከታተል ፍላጎት አሳድሮባታል። በዚህም ዘንድሮ በሚሰጠው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የክረምት ስልጠና በምታገኘው እውቀት ፓይለት የመሆን ህልሟን እውን ለማድረግ እንደሚያግዛት ታምናለች።
"ዙሪያ" የተሰኘው መተግበሪያ የንግድ ስርዓቱን በማቀላጠፍ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና ይኖረዋል - ኢትዮ ቴሌኮም
Jul 12, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ "ዙሪያ" የተሰኘው መተግበሪያ የንግድ ስርዓቱን በማቀላጠፍ፣ የተገልጋዮችን ጊዜና ገንዘብ በመቆጠብ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና ገለጹ። ኢትዮ ቴሌኮም፣ ዳሽን ባንክ እና ኢታ ሶሊዩሽን የንግድ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን የሚያቀላጥፍ "ዙሪያ" የተሰኘ የቢዝነስ አውቶሜሽን ሶሉሽን መተግበሪያ ይፋ አድርገዋል። የኢትዮ ቴሌኮም ችፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና እንዳሉት፣ መተግበሪያው የንግድ ስርዓቱን በማዘመን የተገልጋዮችን ጊዜና ገንዘብ የሚቆጥብ ነው። የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በቀላሉ ለማወቅ እንደሚረዳና ለነጋዴዎች የተሻለ የክፍያ መፈጸሚያ አማራጭ እንደሚሆን ጠቁመዋል። "ዙሪያ" ለአጠቃቃቀም ቀላል እና ፈጣን፣ ደህነንቱ የተረጋገጠ መሆኑንም ጨምረው አንስተዋል። የውጪ እና የሀገር ውስጥ የክፍያ ካርዶችን እንደሚቀበልና የሂሳብ ስራን ቀላል እንደሚያደርግም አስታውቀዋል። በወረቀትና በማሽን ይሰራ የነበረውን የክፍያ ስርዓት ወደ አንድ ወጥ አተገባበር የሚያመጣ መተግበሪያ እንደሆነም ጠቁመዋል። መተግበሪያው የንግድ ስርዓቱንና አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል።
ከሀገር በቀል እፅዋት ለእንስሳት ህክምና የሚያገለግሉ መድሃኒቶችን በምርምር የማፍለቅ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jul 12, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ ሀገር በቀል እፅዋትን በመጠቀም ለእንስሳት ህክምና የሚያገለግሉ መድሃኒቶችን የማፍለቅ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ንጉሴ ደቻሳ ገለጹ። የኢንስቲትዩቱ አመራሮች በእንስሳት ጤና እና ተያያዥ የምርምር ዘርፍ አዳዲስ የእንስሳት መድሃኒቶችና የመመርመሪያ ማሳያ ስራዎችን በተመለከተ በሆለታ ግብርና ምርምር ማዕከል የመስክ ምልከታ አካሂደዋል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ንጉሴ ደቻሳ፥ ኢትዮጵያ ያላት ሰፊ የእንስሳት ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ አልዋለም ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ ኢትዮጵያ ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም እንድታገኝ፤ የእንስሳት በሽታን መከላከል የሚያስችሉ ምርምሮችንና ተያያዥ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የሆለታ ግብርና ምርምር ማዕከልም በምርምር የተደገፉ የተለያዩ የመኖ ዝርያዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለእንስሳት ጤና ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በእንስሳት ጤና ዙሪያ በርካታ የምርምርና የህክምና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ ሀገር በቀል እጽዋት ላይ ተገቢውን ምርምር በማድረግ የእንስሳትን ጤና መጠበቅ የሚያስችሉ መድሃኒቶችንና ኬሚካሎችን በምርምር እያፈለቀ እና ወደ ጥቅም እየቀየረ መሆኑንም ተናግረዋል። የብሔራዊ የእንስሳት ጤና ምርምር አስተባባሪ ዶክተር ቤክሲሳ ኡርጌ፥ በእንስሳት ቆዳ ላይ የሚከሰቱ በሽታዎችን ማከም የሚያስችሉ መድሀኒቶች እና ኬሜካሎች በምርምር መገኘታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይ እነዚህን የምርምር ውጤቶች ወደ ማህበረሰቡ ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል እውቅና ከሚመለከተው ተቋም ለማግኘት እንደሚሰራ ተናግረዋል። የሆለታ ግብርና ምርምር ማዕከል ተወካይ ዶክተር ድሪባ ሁንዴ፥ ማዕከሉ የእንስሳት ዝርያን ከማሻሻል ባለፈ የእንስሳት ጤናን መጠበቅ የሚያስችሉ የጥናትና የምርምር ስራዎች እያከናወነ ነው ብለዋል። ማዕከሉ በአካባቢው በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ለተሰማሩ ዜጎች የተሻሻሉ እንስሳት ዝርያዎችን እንዲያገኙ እያከናወነ ያለው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሆለታ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ከበደ ስለሺ ናቸው። የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በማዕከሉ እየተተገበሩ ለሚገኙ የምርምር ስራዎች ከተማ አስተዳደሩ ተገቢውን እገዛ እንደሚያደርግም ገልጸዋል፡፡ የመስክ ተሳታፊ አመራሮች በማዕከሉ ግቢ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል።
ስፖርት
የአውሮፓ ኃያላኑ ቼልሲ እና ፒኤስጂ የክለቦች ዓለም ዋንጫን ለማንሳት ይፋለማሉ
Jul 13, 2025 14
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ ቼልሲ እና ፒኤስጂ ዛሬ የፍጻሜ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፍጻሜው ጨዋታ ላይ ይታደማሉ። የፍጻሜው ጨዋታ 82 ሺህ 500 ተመልካች በሚያስተናግደው ሜት ላይፍ ስታዲየም ምሽት 4 ሰዓት ላይ ይካሄዳል። ቼልሲ በግማሽ ፍጻሜው የብራዚሉን ፍሉሜኔንሴን 2 ለ 0 አሸንፏል። ፒኤስጂ ሪያል ማድሪድ 4 ለ 0 በመርታት ለፍጻሜው አልፏል። ቼልሲ እና ፒኤስጂ ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 10 የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ፒኤስጂ 5 ጊዜ ሲያሸንፍ ቼልሲ 2 ጊዜ አሸንፏል። 3 ጊዜ አቻ ወጥተዋል። ሁለቱ ቡድኖች ስምንት ጊዜ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተገናኝተው ፒኤስጂ 3 ጊዜ ድል ሲቀናው ቼልሲ 2 ጊዜ አሸንፏል። በቀሪዎቹ ሶስት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርተዋል። አስደናቂው ፒኤስጂ የአሸናፊነት ስነ ልቦናው፣ የተከላከይ መስመሩ ጥንካሬ፣ የአማካይ ክፍሉ ኳስ የመቆጣጠር ብቃት እና ፈጣን የማጥቃት እንቅስቃሴው ከብዙዎች አድናቆት እያስቸረው ነው። የፓሪሱ ክለብ በክለቦች ዓለም ዋንጫ እስከ አሁን ባደረጋቸው ስድስት ጨዋታዎች አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። 16 ግቦችን ሲያስቆጥር ያስተናገደው አንድ ግብ ብቻ ነው። ቡድኑ ከስድስቱ ጨዋታዎች በአምስቱ ግብ አልተቆጠረበትም። የተከላካይ መስመር ክፍሉ ተጋላጭነት፣ የትኩረት ማጣት አጋጣሚዎች እና ግብ የመፍጠር ኃላፊነት በተወሰኑ ተጫዋቾች ላይ የተንጠለጠለ መሆኑ ፒኤስጂ እንደ ድክመት ሊነሱበት የሚችሉ ጉዳዮች ናቸው። ተጋጣሚው ቼልሲ በወጣቶች እና የመጫወት ረሃብ ባላቸው ባለክህሎቶች የተሞላ ነው። የአማካይ ክፍሉ ጥንካሬ እና ሚዛን፣ የታክቲክ ተለዋዋጭነት እና የታክቲክ ተገዢነት እንዲሁም የማጥቃት አቅም የምዕራብ ለንደኑ ቡድን የጥንካሬ መገለጫዎች ናቸው። ቡድኑ በውድድሩ ባደረጋቸው ስድስት ጨዋታዎች አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏልክ። 14 ግቦችን ሲያስቆጥር 5 ግቦች ተቆጥረውበታል። የተከላካይ ክፍሉ የአደጋ ተጋላጭነት፣ ልምድ ማነስ እና የጎል ማስቆጠር ያሉ ችግሮች አንድ ድክመት ይነሱበታል። ፒኤስጂ ከፈረንሳይ ሊግ 1፣ የፈረንሳይ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ እና የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ድሉ በኋላ አራተኛውን ዋንጫ ለማንሳት ይፋለማል። ቼልሲ ከአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ድሉ ላይ የክለቦች የዓለም ዋንጫን ለመጨመር ይጫወታል። ፒኤስጂ ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ ግምቱን ቢውሰድም ዋንጫ ካየ ወደ ኋላ ከማይለው ቼልሲ ጠንካራ ፈተና ይጠብቀዋል። የኢራን እና አውስትራሊያ ጥምር ዜግነት ያላቸው የ47 ዓመቱ አሊሬዛ ፋግሃኒ ተጠባቂውን የፍጻሜ ጨዋታው በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፍጻሜውን ጨዋታ በሜትላይፍ ስታዲየም ተገኝተው እንደሚከታተሉ ተረጋግጧል። የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ለውድድሩ ተሳታፊዎች በአጠቃይ የአንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽልማት አዘጋጅቷል። ውድድሩን የሚያሸንፈው ቡድን የ40 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽልማት ያገኛል። ለፍጻሜ ያለፉ ቡድኖች ለፍጻሜ በማለፋቸው ብቻ 30 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይበረከትላቸዋል።
ሞሮኮ እና ዛምቢያ ለሩብ ፍጻሜ አለፉ
Jul 13, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ማምሻውን ተደርገዋል። በፕሪንስ ሙላይ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አዘጋጇ ሞሮኮ ሴኔጋልን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ያሲን ምራቤት በመጀመሪያ አጋማሽ ጭማሪ ደቂቃዎች ላይ በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠረችው ግብ ቡድኑን ባለድል አድርጋለች። ሞሮኮ በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ ሆና በማጠናቀቅ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች። በዚሁ ምድብ ማምሻውን በተመሳሳይ ሰዓት በኤል ባቺር ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ዛምቢያ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን 1 ለ 0 ረታለች። ራቼል ኩንዳናንጂ የማሸነፊያውን ጎል በ9ኛው ደቂቃ አስቆጥራለች። የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የአጥቂ መስመር ተሰላፊ ፋሎኔ ፓምባኒ በ69ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብታለች። ውጤቱን ተከትሎ ዛምቢያ በተመሳሳይ ሰባት ነጥብ በሞሮኮ በግብ ክፍያ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ሩብ ፍጻሜ ገብታለች። በምድቡ ሶስቱንም ጨዋታ የተሸነፈችው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ከውድድሩ የተሰናበተች የመጀመሪያ ሀገርም ሆናለች። በምድብ አንድ በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ይዛ የጨረሰችው ሴኔጋል ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ ለማለፍ የሌሎች ምድብ ውጤቶችን ትጠብቃለች። ናይጄሪያ ሩብ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያ ሀገር መሆኗ ይታወቃል።
የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
Jul 12, 2025 78
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ ሶስተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ። ከምሽቱ 4 ላይ አዘጋጇ ሞሮኮ ከሴኔጋል በፕሪስን ሙላይ አብደላ ስታዲየም ይጫወታሉ። በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ዛምቢያ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤል ባቺር ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ሞሮኮ አራት ነጥብ በመያዝ ምድቡን በአራት ነጥብ እየመራች ትገኛለች። ሴኔጋል በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛለች። አዘጋጅ ሀገር ሞሮኮ ማሸነፍ ወይም አቻ መውጣት ወደ ሩብ ፍጻሜው ያሳልፋታል። ተሸንፋም ጥሩ ሶስተኛ ሆኖ የማለፍ እድል አላት። ሴኔጋል ካሸነፈች በቀጥታ ሩብ ፍጻሜውን ትቀላቀላለች። አቻ መውጣት ወይም መሸነፍ ሁለተኛ አሊያም ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ እንድታልፍ ሊያደርጋት ይችላል። ዛምቢያ በምድቡ አራት ነጥብ በመሰብሰብ ተመሳሳይ ነጥብ ባላት አዘጋጇ ሞሮኮ በግብ ክፍያ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። ማሸነፍ ዛምቢያ የማንንም ውጤት ሳትጠብቅ ወደ ሩብ ፍጻሜ እንድትገባ ያስችላታል። ተሸንፋ ወይም አቻ ወጥታ በሂሳባዊ ስሌት ቀጣዩን ዙር የመቀላቀል እድል ልታገኝ ትችላለች። ሁለት ሽንፈት ያስተናገደችው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛለች። ማሸነፍ የኮንጎን ምርጥ ሶስተኛ ሆና የማለፍ እድሏን ሊያለመልመው ይችላል።
ታንዛንያ እና ደቡብ አፍሪካ ነጥብ ተጋርተዋል
Jul 12, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት መርሃ ግብር ታንዛንያ እና ደቡብ አፍሪካ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ትናንት ማምሻውን በሆነር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አጥቂዋ ኦፓ ክሌመንት በ24ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠረችው ግብ ታንዛንያ መሪ ሆናለች። የተከላካይ መስመር ተሰላፊዋ ባምባናኒ ምባኔ በ70ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ላይ ያሳረፈችው ጎል ደቡብ አፍሪካን አቻ አድርጓል። የታንዛንያዋ ኤልሳቤት ጆን ቼንጌ በ84ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ሜዳ ተሰናብታለች። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ደቡብ አፍሪካ በአራት ነጥብ የምድቡን መሪነት ከማሊ ተረክባለች። ታንዛንያ በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዚሁ ምድብ ትናንት በተደረገ ጨዋታ ጋና እና ማሊ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ደቡብ አፍሪካ ከማሊ፣ ጋና ከታንዛንያ የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም የመጨረሻ የምድብ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የማከናወኑ ተግባር ይጠናከራል - ሚኒስትር መላኩ አለበል
Jul 12, 2025 75
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የማከናወኑ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ተናገሩ፡፡ ሚኒስትሩና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እንቅስቃሴን የተመለከቱ ሲሆን፤ ችግኝ በመትከልም አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ በዚህ ወቅት ሚኒስትሩ በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተቀናጁ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ከአየር ንብረት ጋር የተስማማ ሁኔታ እንዲኖር የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ስራ እየተስፋፋ ነው። ዛሬም በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተከናወነው የዚህ አካል መሆኑን አንስተው፤ በቀጣይም ይህንን የበለጠ እያጠናከርን እንሄዳለን ብለዋል። ጠንክሮ በመስራትና ኢኮኖሚኖዋን በማሻሻል ኢትዮጵያ እንደምታንሰራራ ያመለከቱት ሚኒስትሩ፤ የምንተክለውም መልካም ዘር ነው፤ የኢትዮጵያን የወደፊት ተስፋን የሚያለምለምና የስራ ባህልን ታሳቢ ያደረገ ነው ሲሉ ተናግረዋል። "በመትከል ማንሰራራት" የሚለው ቁልፍ መልዕክትም እነዚህን ሁሉ ያየዘ በመሆኑ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኢንዱስትሪዎች የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ሀይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ሁሉ ስራ የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የችግኝ ተከላ ልዩ ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል፡፡ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብሩ የሚተከለው ችግኝ ለምግብነት፣ ለፋብሪካ ግብዓትና ለማገዶ ጨምሮ አካባቢው ለኑሮና ለስራ የተመቸ ከማድረግ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ፓርኮች ይህን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል፡፡ የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ አራርሶ ገረመው(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተሰማሩ ከ8 በላይ ካምፓኒዎች የግብርና ምርቶች በማቀነባበር ላይ መሰማራታቸውን ተናግረዋል። ፓርኩን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችል የድጋፍና ክትትል ውይይት መደረጉን ተናግረው፤ ችግኝ በመትከል የፓርኩን ስራ ለማጠናከር የሚያግዝ ዐሻራ ማኖራቸውንም አንስተዋል፡፡ በፓርኩ የስራ ዕድልና የገበያ ትስስርን በመፍጠር እንዲሁም የግብርና ቴክኖሎጂ በማሸጋገር ረገድ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ መኖሩን የገለጹት የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሀይሉ ዬተራ ናቸው፡፡ ከ137ሺህ በላይ አርሶ አደሮች የምርት አቅርቦት ትስስር መፈጠሩንም ጠቅሰዋል፡፡
አረንጓዴ ዐሻራ የነገዋን ኢትዮጵያ ለትውልዱ ምቹና የተሻለች የሚያደርግ ነው
Jul 12, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ ዐሻራ የነገዋን ኢትዮጵያ ለትውልዱ ምቹና የተሻለች የሚያደርግ መሆኑን የነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ሰልጣኞች እና የባለድርሻ ተቋማት ኃላፊዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል፡፡ የነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ሃላፊዎች፣ ሰልጣኞች እና ባለድርሻ አካላት በማዕከሉ ግቢ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። የቀድሞ የአዲስ አበባ ማኅበራዊ ትረስት ፈንድ ዋና ዳይሬክተር አስራት ንጉሤ በዚሁ ወቅት፤ አረንጓዴ ዐሻራ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ከመከላከል ጀምሮ በርካታ ትሩፋቶችን እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በነገዋ የሴቶች የተሃድሶና የልህቀት ማዕከል የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር መከናወኑ ትልቅ ፋይዳ አለው ነው ያሉት። በማዕከሉ ያሉ ሴቶች ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡና ዐሻራቸውን የሚያሳርፉበት እድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በስልጠና ቆይታቸው ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ ስለአረንጓዴ ልማት ተግባራዊ ግንዛቤ እንደሚያገኙበትም አንስተዋል። የነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ምክትል ዳይሬክተር ልኬ ኃይለማርያም በበኩላቸው፤ በዛሬው የአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ-ግብር ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ ችግኞችን ከመትከል ባለፈ ፀድቀው ለፍሬ እንዲበቁ በማዕከሉ ወስጥ የሚገኙ ሰልጣኞችን በማሳተፍ የመንከባከብ ሥራ እንደሚሰራ ገልፀዋል። የማዕከሉ ግቢ በአረንጓዴ ልማት የሚታወቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬው ችግኝ ተከላም ገጽታውን ይበልጥ የሚያጎላ ነው ብለዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ከተሳተፉት ባለድርሻ አካላት መካከል የታፍ ኢነርጂ የቦርድ አባል የሆኑት ኤልሳቤጥ ፈታሂ፤ ድርጅቱ ለምግብነት የሚያገለግሉ የፓፓዬ፣ የአፕልና የአቮካዶ ችግኞችን በነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ግቢ መትከሉን ገልጸዋል፡፡ ችግኞቹ የተተከሉበት ቦታ ለመንከባከብ አመቺ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ችግኞችን እንደሚንከባከቡም ተናግረዋል፡፡ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት የመርኃ-ግብሩ ተሳታፊዎች መካከል ዶክተር ፍስሃ ዋሱ እና እየሩሳሌም አንዷለም በአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ-ግብር ችግኞችን በመትከላቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል። በነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ችግኝ የተከለችው ሰልጣኝ እየሩሳሌም አንዷለም እንደገለጸችው፤ አረንጓዴ ዐሻራ ለመጪው ትውልድ ጉልህ ፋይዳ አለው። በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉት ችግኞች ለፍሬ እንዲበቁ እንክብካቤ እንደምታደርግ ነው የተናገረችው፡፡ ከታፍ ኢነርጂ የመጡት ዶክተር ፍስሃ ዋሱ በበኩላቸው፤ አረንጓዴ ዐሻራ ለትውልዱ ምቹና ሥነ-ምኅዳሯ የተጠበቀ ሀገር ለማስረከብ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። በዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱ ይታወቃል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የአፈር መሸርሽርን በመከላከል ፅዱ እና የተሻላች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያገዘ ነው - ባለስልጣኑ
Jul 12, 2025 66
ሸገር፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር የአፈር መሸርሽርን በመከላከል ጽዱ እና የተሻላች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያገዘ መሆኑን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ገለጸ። ባለስልጣኑ ከኦሮሚያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ በአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በመርሃ ግብሩ የፌዴራል የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ፣ ባለፉት ስድስት ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተሰራው ሥራ ፅዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር ለሚከናወኑ ሥራዎች ጠንካራ መሰረት ጥለዋል ብለዋል። በተያዘው ዓመትም የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሰባት ወራት የሚቆይ ጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ እያካሄደ መሆኑን አስታውሰዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር የአፈር መሸርሽርን በመከላከልና ምንጮች እንዲጎለብቱ በማድረግ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። የተራቆተ የተፈጥሮ ሀብት መልሶ እንዲያገግም ከማድረግ ጎን ለጎን ጽዱና ጤናማ አካባቢን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አስረድተዋል። በመሆኑም ባለስልጣኑ በአሁኑ ወቅት ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች እየተከለ መሆኑን ተናግረዋል። በዛሬው እለትም ከኦሮሚያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ ከሸገር ከተማ አስተዳደር እና ከግል ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት በገላን ክፍለ ከተማ የተካሄደው ችግኝ ተከላ የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን አስረድተዋል። የኦሮሚያ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሴፋዲን ማሃዲ በበኩላቸው በክልሉ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር በተከናወኑ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል። የክልሉ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በአረንጓዴ ልማት ሥራ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑን ገልጸው፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ካለው ፋይዳ ባለፈ ለዜጎች የሥራ እድል መፍጠሪያ እየሆነ መምጣቱን አመልክተዋል። ከመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ክበበው ሙሉነህ ችግኝ ለአካባቢ ውበትና ጽዳት ያለውን ሚና በመገንዘብ በየዓመቱ ችግኞችን በመትከል ዐሻራቸውን እያኖሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላው ተሳታፊ የሮን ተካልኝ በበኩላቸው ለሁሉም ምቹ የሆነች ጽዱና አረንጓዴ ኢትዮጵያ መፍጠር የሚቻለው ዛሬ በሚተከሉ ችግኞች በመሆኑ ሁሉም በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ሊሳተፍ ይገባል ብለዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬታማነት የኢትዮጵያ ማንሰራራት እና ከፍታ አንዱ ማሳያ ነው - ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)
Jul 12, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬታማነት የኢትዮጵያ ማንሰራራት እና ከፍታ አንዱ ማሳያ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ። የግብርና ሚኒስቴር አመራር እና ሰራተኞች "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አውስተዋል። በዚህም እስካሁን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ መተከሉን ገልጸዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ እድገት እያመጣ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፥ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለምግብነት፣ ለአካባቢ ውበት፣ ለደንና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ ችግኞች እየተተከሉ መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮ አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ በተከናወነባቸው አካባቢዎች የችግኝ ተከላ እንዲካሄድ አቅጠጫ በማስቀመጥ እየተተገበረ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በመርሃ ግብሩ ባለፉት ዓመታት ምርታማነት ማደጉን፣ የአፈር መሸርሸር መቀነሱን፣ የደን ሽፋን ማደጉን ጠቅሰው፥ መርሃ ግብሩ ትላልቅ ስኬቶችን እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀግብር መካሄድ ከጀመረ ወዲህ የተተከሉ ችግኞች ምርት መስጠት መጀመራቸውንና ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እያስገኙ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ሀብቷን ለልማት በማዋል የተፈጥሮ ሀብቷን በመጠበቅ ላይ እንደምትገኝ አንስተው፥ የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬትም የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን እና የከፍታ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል። የሸገር ከተማ ምክትል ከንቲባና የግብርና ክላስተር አስተባባሪ ግርማ ኃይሉ በበኩላቸው የአረንጓዴ ዐሻራ ስራ የሸገር ከተማን ጽዱ፣ አረንጓዴ እና ውብ ለማድረግ የተጀመረውን ጥረት የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። በችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ የተሳተፉት በግብርና ሚኒስቴር የሚሰሩት አቶ እስራኤል ሎሃ፥ ዛሬ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች መተከላቸው የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ያረጋግጣሉ ብለዋል። ወይዘሮ በላይነሽ ኩምሳ የተባሉት የመርሃ ግብሩ ተሳታፊ በበኩላቸው ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን በመንከባከብ እንዲጸድቅ የበኩላችንን እንወጣለን ነው ያሉት። የአረንጓዴ ዐሻራ አካባቢ እንዲጠበቅና የተራቆተ መሬት እንዲያገግም በማድረግ በኩል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አቶ ተመስገን ደሳለኝ የተባሉ የመርሃ ግብሩ ተሳታፊ ናቸው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 910
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ። በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1304
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 973
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል። ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1599
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
የህንድ የፈጠራ ማዕከል - ባንጋሎሩ
Jul 2, 2025 428
ቤተልሄም ባህሩ(ኢዜአ) የዴልሂና አግራ ቆይታችንን ጨርሰን ወደ ቀጣይ መዳረሻችን ባንጋሎሩ ከተማ ልንጓዝ ስንሰናዳ አብዛኛው የጋዜጠኛ ልዑክ ያሳሰበው እንደሰም የምታቀልጠውን የአግራ ፀሀይና ሙቀት በባንጋሎሩም ታገኘን ይሆን? የሚለው ነበር። ሆኖም ከዴልሂ ኢንድራ ጋንዲ አየር ማረፊያ ተነስተን ለሶስት ሰዓት ከተቃረበ በረራ በኋላ ያገኘናት ባንጋሎሩ የተለየች ሆነን አገኘናት። ባንጋሎሩ ቀዝቀዝ ባለ አየር ነበር እንግዶቿን የተቀበለችን። በዕለቱ ከክፍሎቻችን ወጥተን በጋራ ወደአየር ማረፊያ የሚወስደንን ትራንስፖርት ስንጠባበቅ ከጋዜጠኛ ቡድኑ ስድስት አባላት ከአጠገባችን እንዳልነበሩ አስተዋልን። የት ጋር እንደተነጣጠልን አላስታውስም። በዚህ ምክንያት ግን የእለቱ ጉዟችን ተሰርዞ ከተማዋን ለማየት ስንዘዋወር የማውቀው ዓይነት እንጂ የተለየ ሙቀት አላስተናገድኩም። የ13 ወር ፀጋ በመባል የምትታወቀው አገሬ ኢትዮጵያ ከዳሎል እስከ ራስ ዳሽን ባላት የመልከዓ ምድር አቀማመጥና ልዩ ልዩ የአየር ጠባይ ሙቀቱንም፣ ቅዝቃዜውንም ማወቃችን እንደዚህ ለአለ አጋጣሚ መልካም ስሜት ይፈጥራል። በተወሰነ ደረጃ በህንድ ያጋጠመኝ የአየር ባህሪ ከአገሬ ጋር ቢመሳሰልብኝ የፈጣሪንና የተፈጥሮን ስራ አጃኢብ ብዬ እንዳልፍ አድርጎኛል። ባንጋሎሩ ከተማ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የህንድ ሲልከን ቫሊ በመባል ትታወቃለች። ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎችም ከመገለጫዎቿ መካከል ናቸው። የጠፈር ጠበብቶቹ - ባንጋሎሩ ደርሰን በመጀመሪያ ያየነው ዓለም በስፔስ ሳይንስ እየሰራች ያለችውና እያስመዘገበችው የምትገኘው ውጤት ማሳያ የሆነውን የህንድ ስፔስ ምርምር ድርጅትን ነው። ተቋሙ የህንድ መንግስት የስፔስ ዲፓርትመንት አካል ሲሆን፤ ዶክተር ቪክራም ሳራብሃይ በተሰኙ ባለራዕይ በ1962 የተወጠነና አሁን ላይ በዘርፉ ተገዳዳሪ መሆን የቻለ ነው። የተቋሙ ዓላማ የስፔስ ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመተግበር ለተለያዩ አገራዊ ጥቅሞች ማዋል መሆኑን ተከትሎ የሳተላይት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማምረት ስራን ጨምሮ ከአገሩ አልፎ ለሌሎች አገራትም በዘርፉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። የተደረገልን ገለፃ አብዛኛውን ጋዜጠኛ ያስደመመ ነበር ከገለፃ በኋላ በጋዜጠኞች የተነሳው ሃሳብም ህንድ በስፔስ ዘርፍ ያላት ልምድና ያከናወነችው ተግባር በቀጣይም ልትሰራ የወጠነቻቸው ሃሳቦች የአገሪቱን መዳረሻ የተለሙ በአገራቸው እንዲተገበር የሚናፍቁት መሆኑን ነው። ተቋሙ በዘርፉ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን የሚያጠናክር መሆኑን ከተደረገልን ገለፃ ተገንዝበናል። በሳይንስ፣ ኢንጂነሪንግና አስተዳደር ምሁራንን በማስተማር እያበረከተ ያለው የህንድ የሳይንስ ኢንስቲትዩት በባንጋሎሩ ከጎበኘናቸው መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የተውጣጡ ተማሪዎችን የሚያስተምርና ከተቋማት ጋርም በዘርፉ የሚሰራ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ከጅማ፣ በተግባር ለመቀየር ሲታትሩ የስታርት አፖችን የምርት ውጤቶቻቸውን ሲፈትሹና ሲሞክሩ ተመልክቻለሁ። በኢትዮጵያም አሁን ላይ ለስታርት አፖች በተሰጠው ትኩረትና በተፈጠረው ምቹ ስነ ምህዳር የፈጠራ ውጤቶች እያደጉና እየተበራከቱ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። እንደ አዳማና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት የተማሪዎችን ፈጠራ ወደ ውጤት ለመቀየር እየተጉ መሆኑና የስታርት አፕ ኤግዚቢሽንና የሰመር ቡት ካምፖች ፈጠራን ምን ያህል እያበራከቱ መሆናቸው በጉብኝቱ ወቅት ወደ አዕምሮዬ የመጣ የአገሬው ህዝብ በውጤት የታጀበ ጥረት ነው። ከአራት አስርት ዓመታት በላይ በባዩቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘው ባዮኮንም ከባላንጎሩ የጉብኝት መዳረሻችን መካከል የሆነና አስፈላጊ መድሀኒቶችን የሚያመርትና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይም እየሰራ ያለ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተጠቃሚ ናቸው። ከ120 በላይ በሆኑ አገራት ለስኳርና ካንሰር ህመም የሚያገለገሉ መድሀኒቶችን በማምረትና በማሰራጨት ለህሙማን ፈውስና ለጤናው ዘርፍ ስርዓት አስተዋፅኦ እያበረከተም ይገኛል። የተቋሙ ላቦራቶሪና ዘመኑን የዋጀና ደረጃውን የጠበቀ ማምረቻ ፋብሪካን መጎብኘቴ አለም በፋርማሲዩቲካልስ ዘርፍ ያለችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። የባንጋሎሩ ቤተመንግስት - ይህን ቤተ መንግስት ማስቃኘቴን ከመጀመሬ በፊት በስፍራው ካስገረመኝ ነገር ላወጋችሁ ወደድኩ። ቤተ መንግስቱን ለመጎብኘት ያቀናነው በእለተ ሰኞ ነበር። ሆኖም ምድረ ግቢውን ቃኝተን ስለህንፃው ሰምተን ከመመለስ ውጪ ወደ ውስጥ አልዘለቅንም። ለምን? ለሚለው ምላሹ በዚህ ስፍራ "ሰኞ የእረፍት ቀን ናት" ነው። እንዴት ካላችሁ ቤተ መንግስቱ ቅዳሜና እሁድ በበርካታ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑን ተከትሎ በስፍራው ለሚሰሩ ሰራተኞች የእረፍት ቀናቸው ሰኞ በመሆኑ ነው። የቤተ መንግስቱ ምድረ ግቢ ሰፊና ልምላሜ የተላበሰ ሲሆን፤ የሚያምርና ለዓይን የሚስብ ኪነ ህንፃ ያለው ነው። አሰራሩና ውጥኑም እንደሚከተለው ነው። በዎዲየር ስርወ መንግስት ንጉስ ቻማራጃ ዋዲያር ወደ እንግሊዝ ባደረጉት ጉዞ በለንደን ዊንሶር ግንብ ይደነቃል። ተደንቆም አልቀረ የባንጋሎሩ ቤተ መንግስትን በተመሳሳይ ሁኔታ ይገነባል። ይህ ቤተ መንግስት በተወሰነ መልኩ የመካከለኛው ዘመን የኖርማንሲና የእንግሊዝ ግንቦችን ይመስላል። ቪድሃና ሶውዳ የካራንታካ ህግ አውጪ አካል መናገሻ በጉብኝታችን ያየነው ሌላው መዳረሻ ስፍራችን ነው። የህግ አውጪና የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የያዘው ይህ ህንፃ ህንድ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ በራሷ መሀንዲስ የሰራችው የመጀመሪያው ህንፃ መሆኑ ተገልፆልናል። የህንፃ ግንባታ ጥበብ ማሳያ፣ የፖለቲካ መናገሻ እንዲሁም የባህል ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። እንደአጠቃላይ በቆይታዬ የተመለከትኩት የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ማበረታቻ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራ ኢትዮጵያ እያከናወነች ካለው የኮሪደር ልማትና ስታርት አፕን የማበረታታት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ምቹነት ስራዎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ነው። በህንድና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ዘመናትን የተሻገረ፤ ለሁለት ሺህ ዓመታት የዘለቀ መሆኑን የታሪክ መዛግብት ያሳያል። የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት በአክሱም ስርወ መንግስት ኢትዮጵያና ህንድ በአዱሊስ ወደብ በኩል የንግድ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያ ቅመማ ቅመምና ሐርን ከህንድ ትገበይ ነበር። ህንድ ደግሞ ወርቅና የዝሆን ጥርስን ከኢትዮጵያ ትሸምት ነበር። ህንድ ከንግድ ልውውጥ ባሻገር በኢትዮጵያ ኪነ ህንፃ ግንባታ ላይ አሻራዋን አኑራለች። በኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍም ትልቅ አበርክቶ ያላት አገር ናት። ህንድ ነፃነቷን ካገኘችበት እኤአ 1948 አንስቶ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት ኢትዮጵያና ህንድ ሌላው የሚያመሳስላቸው ነገር ሆኖ ያገኘሁት የአምራች ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያከናወኑ ያሉት ንቅናቄ ነው። ህንድ እ.አ.አ ከ2014 ጀምሮ የአምራች ዘርፉን ለማበረታታት "ሜድ ኢን ኢንዲያ" በሚል ለአስር ዓመት የተገበረችውና በርካታ ለውጥ የተመዘገበበት ንቅናቄ በኢትዮጵያ ከ2014ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ካለውና የሃገር በቀል ምርቶች እና አምራቾችን ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪያል ማህበረሰብ ግንባታን ማሳደግ ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢ መፍጠር እና የጥናት እና ምርምር ችግር ፈቺነትን ማሳደግን ዓላማ ካደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጋር የተመሳሰለ ነው። ንቅናቄ በኢትዮጵያ መተግበሩ ዓመታዊ የዘርፍ ዕድገት፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና ገቢ ምርት በመተካት በኩል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑም ይታወቃል። በህንድ ተዘዋውሬ በተመለከትካቸው ከተማዎች ባሉ ጎዳናዎች ከታዘብኩት ነገር ሰዎች ከሱቅ ለሚገበያዩት ነገር ሳይቀር በዲጂታል መንገድ ክፍያ መፈፀማቸውን ነው። በባጃጅና በሞተር የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘትም ጭምር ሞባይሉን በመጠቀም “ይህ ቦታ የት ነው?” ሳይል ያሻዎት ስፍራ መድረስም ሌላው ትዝብቴ ነው። ይህ ነገር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትኩረት አግኝተው እየተሰራባቸው ካሉት የዲጂታል ክፍያና ዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ መርሃ ግብር ጋር የሚመሳሰል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በቆይታችን ልክ እንደአትሌቶቻችን ሁሉ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርጎ የሚያስነሳውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝናና ክብር ለማስተዋል ችያለሁ። ፀጉረ ልውጥ መሆናችንን የተገነዘቡ በገበያ ማዕከላት የሚያገኙን እንዲሁም በምንጎበኛቸው ተቋማት የምንተዋወቃቸው ህንዳውያን "ከየት ናችሁ?" ብለው ሲጠይቁ፤ ለእኔና አንድ ከሌላ መገናኛ ብዙሃን የሄድን "ከኢትዮጵያዊ" ስንል የሚከተልልን ምላሽ "አሃ የኢትዮጵያ አየር መንገድ" የሚል ነው። ይህም አየር መንገዱ ስሙ ከኢትዮጵያ ተሰናስሎ የሚጠራ የአገሪቷ መታወቂያ ተቋም መሆኑን ያስገነዘበኝ ነው። ከህንዳውያን ጋር ብቻ ሳይሆን አብረን ከተጓዝን ጋዜጠኞች አንዱ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእናንተ የብቻ ሳይሆን እኛንም እንደራሳችን ሆኖ እያገለገለን ያለ የጋራ አየር መንገዳችን ነው" ሲል ነው የገለፀው። ይሄ ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገር ኩራት ብቻ ሳይሆን መለያ ምልክትም ጭምር መሆኑን የተረዳሁበት አጋጣሚ ነው። በቀናት ቆይታዬ በእንግዳ አክባሪነታቸውና በለገሱን ፍቅርና እንክብካቤ ከአገሬ የራቅኩ ያህል ሳይሰማኝ ብቸኝነትን ሳላስተናግድ እንደውም እየናፈኳቸው እንድመለስ ላደረጉኝ ህንዳውያን በከበረ ሰላምታ ላመሰግን እወዳለሁ።
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 449
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል። ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል። የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው። የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው። ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 984
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች። የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች። ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ። ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 1102
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 3370
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት
Dec 16, 2024 2809
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2987
የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል። ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 4106
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2670
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2368
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3821
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል። በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል። የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
መጣጥፍ
ከሮም እስከ አዲስ አበባ
Jul 11, 2025 154
ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ይካሔዳል። የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ኢንቨስትመንት እና ፋይናንስ፣ የምግብ ስርዓት ሽግግር ሁለንተናዊነትና የተገቡ ቃሎችን ከመፈጸም አንጻር ያለውን የተጠያቂነት ስርዓት ማጠናከር ጉባኤው ትኩረት ያሚያደርግባቸው ሀሳቦች ናቸው። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተምግብ ጉባኤ በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በጣልያን ሮም የተካሄደው የመጀመሪያ የተመድ ስርዓት ምግብ ላይ የተገቡ ቃሎች ትግበራ ሂደትን መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ነው። በመጀመሪያው ጉባኤ ላይ የ182 ሀገራት ተወካዮች፣ 21 የሀገራት መሪዎች እና 126 ሚኒስትሮችን ጨምሮ 3 ሺህ 300 ተሳታፊዎች ታድመውበታል። በጉባኤው ላይ የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሀገራት እና ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ስድስት የትኩረት አቅጣጫዎችን ይፋ አድርገው ነበር። የምግብ ስርዓት ስትራቴጂዎችን ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር፣ ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓት አስተዳደር መገንባት፣ በጥናት፣ ዳታ፣ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ ሁሉን አቀፍ የእቅድ ዝግጅት እና ትግበራን ማጠናከር፣ በምግብ ስርዓት ውስጥ የንግዱ ማህበረሰብ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የአጭርና የረጅም ጊዜ የአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ ከትኩረት አቅጣጫዎቹ መካከል ይጠቀሳሉ። ኢንቨስትመንት፣ የበጀት ድጋፍ እና የእዳ አስተዳደር ሌላኛው የትኩረት መስክ ነው። በጉባኤው ላይ 300 ገደማ በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የምግብ ስርዓት ሽግግርን እውን ለማድረግ ቃል መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያመለክታል። በተለይም እ.አ.አ 2030 የማይበገር፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የምግብ ስርዓት መገንባት እንዲሁም ምግብ ለሁሉም የሚለውን ግብ ለማሳካት ጥረት እንደሚያደርጉ ሀገራት ቃል ገብተዋል። ሁሉን አሳታፊ ነው በሚል አድናቆት ያገኘው ጉባኤው በስርዓት ምግብ ላይ ግንዛቤን ከማሳደግ እና አቅምን ከመገንባት አንጻር ውጤታማ እንደነበር ይነሳል። የምግብ ስርዓት ሽግግር አንገብጋቢና ጊዜ የማይሰጥ ጉዳይ እንደሆነም በጉባኤው ተወስቷል። ኢትዮጵያም በስርዓተ-ምግብ ጉባኤው ላይ የነበራት ተሳትፎ ስኬታማ ነበር። በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ውጤታማ እንቅስቃሴዎችን የሚያሳዩ ልምደችን አቅርባለች። በጉባኤው ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ግብርናን በማዘመን የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና በስርዓተ ምግብ ሽግግር ለማምጣት እየወሰደች ባለው የፖሊሲ እርምጃና ውጤቶች ዙሪያ ገለጻ አድርገውም ነበር። ኢትዮጵያ የኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት፣ ለየስነ ምህዳሩ ተስማሚ የሆኑ የተሻሻሉ ዝርያዎችን፣ አነስተኛ ቴክኖሎጂዎችንና ሌሎች ግብአቶችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለኢኮኖሚው ዕድገት የላቀ አበርክቶ እንዲኖረው እየሰራች መሆኑንም አንስተዋል። በአረንጓዴ አሻራ፣ በበጋ መስኖ በተለይም በበጋ ስንዴ ምርት እና በሌማት ትሩፋት እየተገኙ ያሉ ውጤቶችን ለጉባኤው አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የስራ እድል ፈጠራን ለማበረታታትም ሆነ በስርዓተ-ምግብ ሽግግር ለማድረግ አዲስና የተለየ የፋይናንስ ሞዴል ያስፋልጋል በማለት በአጽንኦት ተናግረዋል። ዘላቂና አካታች የስርዓተ ምግብ ሽግግር አቅጣጫዎች ጥሩ አፈጻጸም የታየባቸው ቢሆንም በፋይናንስ አቅርቦት፣ በዓለም አቀፍ ትብብር፣ በአየር ንብረት ለውጥና በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመቋቋም በትብብር በመስራት በኩል በርካታ ችግሮች መስተዋላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የገለጹት። በመሆኑም ሀገሮች በስርዓተ ምግብ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በአነስተኛ እርሻ ስር-ነቀል ለውጥ በማምጣት ሽግግሩን ማፋጠን እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፅንኦት አንስተዋል። ለዚህም የሴቶችና የወጣቶች ተሳትፎን እንዲያሳድጉና ለግብርና ቴክኖሎጂ መስፋፋት እንዲሰሩ ጠይቀዋል ። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ-ምግብ ጉባኤ የመጀመሪያውን ጉባኤ መነሻ በማድረግ በተለያዩ አጀንዳዎች ይመክራል። ቀዳሚ ትኩረቱ ከመጀመሪያው ጉባኤው በኋላ የምግብ ስርዓትን አስመለክቶ ያሉ ለውጦች ምንድን ናቸው? የሚለው ነው። በጉባኤው ላይ ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን አስመልክቶ ያገኟቸውን ስኬቶች እና የጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ሪፖርት ያቀርባሉ። በተለይም የምግብ ስርዓት ሽግግሩ ሁለንተናዊነት እና ሁሉን አሳታፊነት ዋንኛ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ሁለተኛው የጉባኤው አጀንዳ በመንግስታት፣ የምግብ አምራቾች፣ የንግድ ማህበረሰቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር ነው። የባለድርሻ አካላት ትብብር መጠናከር የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንዳለው ታምኖበታል። በተጨማሪም ሀገራት እና ተቋማት በሮሙ ጉባኤ የገቧቸው ቃሎች የደረሱበትን ደረጃ የሚገመገም ሲሆን ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎም ይጠበቃል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት እና የኢንቨስትመንት መጠንን መጨመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ጉባኤው ይመክራል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር ስራዎች በአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ፣ አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም እና ሀገር በቀል የፋይናንስ መሰብሰብ አቅምን ማጎልበት ላይ ምክክሮች ይደረጋሉ ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ በሮም በነበረው ጉባኤው ላይ ይፋ ያደረጓቸው ስድስት የትኩረት መስኮች አፈጻጸም ግምገማ ሌላኛው አጀንዳ ነው። በአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ የሚካሄደው ሁለተኛው የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ የሀገራት መሪዎች እና ተወካዮች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ አርሶ አደሮች፣ አምራቾች እና የምግብ ስርዓት ሽግግር ተዋንያንን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። በጉባኤው ላይ ከዋናው ሁነት ጎን ለጎን የምግብ ስርዓት ትራስፎርሜሽን እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን አስመልክቶ በርካታ የጎንዮሽ ስብስባዎች ይደረጋሉ። ኢትዮጵያ በምግብ ስርዓት ሽግግር ያከናወናቸውን ስራዎች አስመልክቶም በጉባኤው ተሳታፊዎች የመስክ ምልከታ ይደረጋል። ኢትዮጵያ በስርዓት ምግብ ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እና በግብርናው ዘርፍ ባደረጋቻቸው ሀገር በቀል ሪፎርሞች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ጉባኤውን እንድታስተናግድ የተመረጥችባቸው ምክንያቶች ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር እየተወጣች ያለው የመሪነት ሚና እና በማደግ ላይ ከሚገኙ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ተምሳሌት የሆነች ሀገር መሆኗ ተመድ ዓለም አቀፉን ከፍተኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ እንዲያደርግ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማሳካት እያከናወነች ባለው ተግባር ዙሪያ ተሞክሮዋን ለዓለም ማህበረሰብ የማስገንዘብ ስራ ታከናውናለች። ተባባሪ አዘጋጇ ጣልያን እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ በምግብ ስርዓት ሽግግር ውጤታማ ተሞክሮ ያላት ሀገር ናት። የደቡብ አውሮፓዊቷ ሀገር ከኢትዮዮጵያ ጋር በመሆን ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን እየሰራችም ትገኛለች። ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎች ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እየጠበቀች ትገኛለች።
በቻይና ይህም አለ!
Jul 8, 2025 242
በአብነት ታደሰ በርግጥ ከዓለማችን የጥንት ስልጣኔ ምድሮች አንዷ ናት- ቻይና። በታሪክ ገጾች ‘የግኝት ምድር’(Land of Invention) የሚል ተቀፅላ የሰፈረላት የሺህ ዘመናት ባለታሪክ ሀገር። የጥንት ቻይኖች አያሌ ‘ግኝቶችን’ ለዓለም አካፍለዋል። ወረቀት ፈብርከው ዘመናቸውን ጽፈዋል፣ ማተሚያ ቁስ ፈጥረው አትመዋል፤ ኮምፓስ ፈልስመው አቅጣጫ ጠቁመዋል።በ221 ዓመተ-ዓለም አንድ ወጥ ስርወ መንግስት መስርተው በሀገረ መንግስት የታሪክ ዑደት ከፍታንም ዝቅታንም አይተዋል። በቻይና አያሌ ስርወ መንግስታት ተፈራርቀዋል። ቻይናውያን ክፉውንም ደጉንም ችለው አልፋዋል። የሕዝቡ ጽናት፣ ጥበብ፣ ቱባ ባህል፣ ታሪክና ብልሃት በቻይና ግንብ ይመሰላል። ግንቡም ዝም ብሎ የጡብ ክምር አይደለም፤ የመሰረተ-ጽኑነታቸው ትዕምርት(symbol) እንጂ። ሲሶውን ሕዝቧ በያንግትዝ ወንዝ ተፋሰስ ጉያ አቅፋ፣ ጥንተ ማንነቷን ሸክፋ ዕልፍ ዘመናትን ተሻግራለች። የቻይና ስርወ መንግስታት ከስመው የዛሬዋ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ ቻይና ከተመሰረተች ገና አንድ ምዕተ ዓመቷ ነው። ቅድመ ልደተ ክርስቶት በ221 ዓመተ-ዓለም የተመሰረተው ወጥ-ስርዎ መንግስት በመልከ ብዙ ምክንያቶች ተዳከመ። በፈረንጆቹ 1912 የመጨረሻው የቻይና ስርዎ መንግስት ተንኮታኮተ። ዘመናዊቷ የቻይና ሪፐብሊክ በዚህ ዘመን ተመሰረተች። ዳሩ ለውጡ አልጋ በአልጋ አልሆነም። ለሺህ ዘመን የጽኑ ስርዓተ መንግስት ባለቤቷ ሀገር ቻይና በአስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት ታመሰች። ወረራንም፣ ዕልቂትንም አስተናገደች። በዘመኑ ማኦ ዘዶንግ የሚባል ባለራዕይ መሪ በቻይና ምድር ተነሳ። አርቆ አሰበ፤ ሀሳቡንም አሰረጸ፤ በዓላማ ጸንቶ ክፉ ዘመን ተሻገረ። ማኦ እና ተከታዮቹ ለቻይና ትንሳኤ ታተሩ። በጽናት ታገሉ። ለመስዕዋትነት ቆርጠው ተነሱ፤ ዋጋም ከፈሉ። በአውሮፓዊኑ ዘመን አቆጣጣር በ1949 የዛሬዋን የቻይና ሕዝባዊ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ መሰረተ። ሃሳቡን ወደ ፖሊሲ ቀየረ፤ ተገበረውም። ቻይናን በኢንዱስትሪና ግብርና ምርት በንቅናቄ የማስፈንጠር ፕሮግራምንም (Great Leap Forward) ገቢራዊ አደረገ። ሆኖም ፖሊሲው በአንዴ ፍሬ አላፈራም። በወቅቱ በተፈጥሯዊና በሌሎች ምክንያቶች ቻይና በረሀብ ጠኔ ተመታች። ቻይናዊያን ተራቡ፤ ጎረቤት ሀገራትን ደጅ ጠኑ፤ ታላቁን ረሀብ መሻገር ያልቻሉ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቻይናዊያን በረሀብ አለቁ። በቻንግሻ የሚገኘው የማኦ ዘዶንግ ግዙፍ ሐውልት መራራ ጽዋን ተጎነጩ። የሀገሪቷ መሪ ማኦ ዘዶንግ በወቅቱ ፈተና ተስፋ ሳይቆርጥ ሀገር አሻጋሪ ፖሊሲውን ገቢራዊ አደረገ። ልመናን ለትውልድ ላለማውረስ፣ ንቅዘትን(ሙስናን) ነውር የሚያደርግ ስርዓት አጸና። ስራን ወንጌል፤ ሙስናን ወንጀል ያደረገ ጽኑ ስርዓተ መንግስት ገነባ። ከራሷ አልፋ ለዓለም የተረፈችዋን የዛሬዋን ቻይና በጽኑ መሰረት ላይ አነበረ። የዛሬዋ ቻይና ከዓለማችን ቁንጮ ልዕለ ሃያል ሀገራት አንዷ ናት። ከራሷ አልፋ ለዓለም ተርፋለች፤ የቻይና ቴክኖሎጂ ምጥቀትና ርቀት ዓለም ጉድ አሰኝቷል። በቅርቡ ሀገረ ቻይናን ከጎበኙ ጋዜጠኞች አንዷ ሆኜ ‘መልክዓ ቻይና’ን በወፍ በረር ቃኘሁ። በዚህ ማስታወሻዬ በቻይና የቴክኖሎጂ ልህቀትና ምጥቀት ላይ ብቻ አተኩራለሁ። ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ህዝብ ባላት፣ በ14 ሀገራት በምትዋሰነው፣ በአንድ ኮሚኒስት ፓርቲ በምትመራው ሀገር ቻይና በነበረኝ የ15 ቀናት ቆይታ ቻይና እንደ ጥንተ ታሪኳ ሁሉ በዘመኑ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ላይ ያላትን የመራቀቅ ጥግ ታዘብኩ። ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን የመቅደም እሽቅድድሟ ‘አጃይብ’ ያሰኛል። በሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና በማዕከላዊ ቻይዋ በምትገኘው የሁናን ግዛት ዋና ከተማ ቻንግሻ ምልከታዬ ቻይና ’ከተባለላት በላይ’ የቴክኖሎጂ ምጥቀቷ አስደንቆኛል። ምናልባትም የመጀመሪያ ጉዞዬ መሆኑም ነገሩን በአንክሮት እንድመለከት ሳያስገድደኝ አልቀረም። የሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከ22 ሚለዮን የሚልቅ ህዝብ በጉያዋ የታቀፈችው ታላቋ ቤጂንግ ከተማ ከዓለማችን ግንባር ቀደም የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህል፣ የቱሪዝምና የዲፕሎማሲ ማዕከላት አንዷ ናት። የአዲስ አበባ እህት ከተማ በዚህ ወቅት ሞቃታማ አየር ጸባት አላት። ቤጂንግ የ21ኛው ክፍል ዘመን የኪነ ህንፃና ክትመት ቴክኖሎጂ ያበበች ብቻ አይደለችም፤ ይልቁኑም በዛፎች ሀመልማላዊ ገጽታ የተላበሰች ውብ መዲና እንጂ። በሕንፃዎችም፣ በዛፎችም የተደነነች ከተማ። በተፈጥሮ የበቀሉ የሚመስሉ ሰማይ ታካኪ ሕንጻዎች፤ የመንገድ መሰረተ ልማት ስፋት፣ ጽዳትና ጥራት ‘ኩልል’ ያለች፣ ‘ምልል’ የምታደርግ ከተማ ያደርጋታል። ቤጂንግ ከተማ ከዘመናችን አስደናቂ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አንዱ በሆነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ) ሕይወትና ኑሮን እንዴት እንዳቃለለ የቤጂንግ የዕለት ከዕለት ክዋኔ ሁነኛ ማሳያ ነው። ቻይኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ተጠበዋል፤ መጠበብ ብቻም ሳይሆን ኑባሬያቸውን ሰው ሰራሽ አስተውሎት መር አድርገዋል። ከሮቦት መስተንግዶ እስከ ሰው ሰራሽ ፀሐይ መራቀቅ ይስተዋላል። ካረፍኩበት ሆቴል (15ኛ ወለል ላይ ከሚገኘው መኝታ ክፍሌ) ሆኜ ያዘዝኩት ምግብ በቅጽበት አስተናጋጇ ‘ከች’ ብላ ትደውላለች። ፍጥነቷ ስትገረም፤ አስተናጋጆች ሮቦቶች መሆናቸውን ስትመለከት ይበልጥ ትደነቃለለህ። በክፍሌ ውስጥ ማብሪያ ማጥፊያ ስጫን መጋረጃው ሲከፈት መደንገጤን አልሸሽግም፣ ከምሽቱ 3 ሰዓት ፀሐይ አለመጥለቋን ስመለከት ‘የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ወጣች እንዴ?’ ማለቴ አልቀረም። በነገራችን ላይ የቻይና የሰው ሰራሽ ፀሐይ ሳይንሳዊ ፈጠራ ሁለት ግዜ ተሞክሮ ያለምንም እንከን እንደሚሰራ ነግረውናል። የሰው ሰራሽ ፀሐዩ ሃይድሮጅን እና ዱተሪየም ጋዞችን እንደ ሀይል ማመንጫ ነዳጅነት በመጠቀም ንጹህ ኢነርጂን ለማመንጨት ታስቦ ዲዛይን እንደተደረገና ሰው ሰራሽ ፀሐይ በርሐን ከተፈጥሮ ፀሐይ 13 እጥፍ ያክል ሙቀት እንደሚያመነጭም ሰምተን ተደንቀናል። የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ፕሮጀክት የሥራ ሰዓትን ከ13 ሰዓት ወደ 24 ሰዓት ለመጨመርና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብ የሰነቀ ነው። በቻይና በሰዉ ቅርፅ የተሰሩ ሮቦቶች በእግር ኳስ ጨዋታዎች ተወዳጅነት አትርፈዋል። ቤጂንግ የሚገኘው ሂዩማኖይድ የተሰኘ የሮቦት ቡድን የሰራቸው ሮቦቶች አመርቂ ውጤት ከራቀው የሀገሪቷ እግር ኳስ ቡድን ይልቅ የሀገሬውን ቀልብ እንደሳቡ ይነገራል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት በታገዘ የሮቦቶች ውድድር አያሌ ቻይናዊያን ይታደማሉ። ሮቦቶቹ በጨዋታ መሐል ቢወድቁ በራሳቸውን ይነሳሉ፤ ቢጎዱም ከሜዳ የሚወጡበት ስርዓት ተዘርግቷል። የታላቋ ቻይና ሰዎች ቴክኖሎጂን ከችግር መፍቻነት ወደ መዝናኛነትም አልቀውታል። በሀገራችን እንደ አዲስ ቴክኖሎጂ በንግዱ ስርዓት ውስጥ እየተዋወቀ ያለው የፈጣን ምላሽ መለያ ወይም ኪው አር ኮድ(Quick Response code) በቻይና ዕለታዊ ከዋኔዎች ቅንጦት አይደለም። በቻይና ማንኛውም ግልጋሎት በዚህ በዲጂታል ስርዓት ይከወናል። እንደሌሎች ስልጡን ሀገራት ሁሉ በንክኪ የሚደረግ ገንዘብ ዝውውር ቀርቷል። በቤጂንግ ጎዳናዎች በኪው አር ኮድ(QR Code) በሚንቀሳቀሱ ሞተር ሳይክሎችን በየመንገዱ ተሰድረዋል፤ የፈለገ መንገደኛ ሳይክሎችን በመጠቀም ወደ ፈለገበት ስፍራ ተንቀሳቅሶ ክፍያውን በኪው አር ኮድ ከፍሎ ይሄዳል። ሌላውም እንዲሁ። በአዲስ አበባ መኖሪያ ሰፈሬ የነበሩ ሳይክሎኝ ከደጃችን ደብዛቸው እንደጠፋ ሳስብ በቻይኖች ብልሃት፣ ታማኝነትና የከተሜነት ልህቀት ቀናሁ። በርግጥ በቻይና ኪው አር(QR) ኮድ ለተገለገልንበት መክፈያ ብቻ ሳይሆን ለልመናም መዋሉን ሲመለከቱ ፈገግ ሊሉ ይችላሉ። በቻይና ይህም አለ በማለት። በርግጥ በቤጂንግ የሰው እጅ ከሚያይ ይልቅ ጆሮቸውን ቢቆጥርጣቸው የሚሰሙ የማይመስሉ አዛውንቶች ሳይቀር በስራ ላይ ተጠምደው ይስተዋላሉ። ከቻይናውያን ጋር ለመግባባት በተለይም በንግድ ማዕከላት የቻይንኛ ቋንቋ መረዳት ግድ ይላል። “ሃው ማቺ፣ ጉዳ ጉዳ፤ ሺሼ፣ ኢ፣ አር…” እና መሰል ቃላት ማወቅ ይበጃል። ከዚህ ባለፈ በምልክት መግባባት አልያም በቋንቋ ተርጓሚ መተግበሪያ መጠቀም ያሻል። የቻይና ሰራሽ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምርቶች በራሳቸው ብራንድ፣ ቋንቋና መልክ እየተመረቱ በተመጣጣሽ ዋጋ ለህዝቦቿ ተደራሽ እየተደረጉ ነው። የቻይና የራስ-በቅነት ጥረት ያስቀናል። በቴክኖሎጂ፣ በባሕልና በኢኮኖሚ ተጽዕኖ ተላቀው በራሳቸው ለመቆም የሄዱበት ርቀት ግሩም ነው። ግብይቶች በራሳቸው ገንዘብ ብቻ ይከወናል። በወቅቱ ምንዛሬ አንድ የአሜሪካ ዶላር ሰባት የቻይና ገንዘብ(ዩዋን) ነው። ከምዕራባዊያን ማህበራዊ ትስስር ገጾች(ለምሳሌ ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክ) በሕግ በማገድ የራሳቸውን መተግበሪያ አበልጽገው ገቢራዊ አድርገዋል። ‘ዊቻት’ የተሰኘው መተግበሪያ ሁሉም ቻይናውያን መገልገያ ነው። ከቤጂንግ ሌላ ያስደነቀችኝ ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከተማ ነች። ቻንግሻ ስመ-ብዙ ነች። ከሶስት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ ጠገቧ የሁናን ግዛት ርዕሰ መዲና ቻንግሻ ‘የከዋክብት ከተማ’ ትሰኛለች። በነገራችን ላይ ማኦ ዘዶንግ ትውልዱ ሁናን ግዛት ውስጥ ነው። ቻንግሻ በስራ ከተማነቷ ‘የማታንቀላፋው መዲና’ ትባላለች። በመዝናኛ ስፍራነቷ ‘የተዝናኖት መነሃሪያ’ የሚል ተቀጥላ ስም አላት። ‘የሚዲያ ጥበብ’ ስፍራም ትሰኛለች። በኢንዱስትሪ፣ በጥንታዊ ሐውልቶች፣ አብያተ መቅደሶች፣ ታሪካዊ ስፍራዎች መገኛ በመሆኗ በቱሪስቶች ተወዳጅ ከተማ ናት። ትናንትና ዛሬን ያዋደደች፣ ታሪክና ባህል ባዛነቀችዋ ቻንግሻ የአምስት ቀናት ቆይታዬ ብዙ ገጽታዋ አስደምሞኛል። የሻንግ ወንዝን ተንተርሳ፣ በተራራማ፣ በሜዳማና ኮረብታማ መልክዓ ምድር በማዛነቅ የተቆረቆረች በመሆኗ የስብት ማዕከል ሆናለች። እንደ ቤጂንግ በደን የተከበበች፣ በዘመነኛ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች እና በታሪካዊ ኪነ ሕንጻዎች የተጌጠች ከተማ ናት። ከዚህ ባሻገር የአምራች ኢንዱስትሪዎች መናገሻም ናት። የምቹ ከተሜነትና ጠንካራ የስራ ባህል በግላጭ የሚስተዋልባት ከተማ። የዓለማችን ገዙፉ በጣም ሞቃታማ አየር ጸባይ ባላት ቻንግሻ ሌት ከቀን ይሰራል። ፋብሪካዎቿ አይተኙም። ሌትና ቀኑ የሚታወቀው በሰዓት ብቻ እንጂ የስራና የንግድ ድባቡ እኩል ነው። ብርሃናማዋ ቻንግሻ ‘የቻይዊያን መስቀል’ በተሰኘው በቀይ በተቀለመው መስቀልም ትታወቃለች። በርግጥ ከዓለማችን ግዙፍ ማማዎች አንዱ የሆነው ሕንጻም መገኛ ናች። በጥቅሉ የቻይና ጉብኝት ትዝብቴ የገናና ታሪክ ባለቤቷ ሀገር ከባድ ውጣ ውረዶችን አልፋ ዛሬ ዓለምን እየቀደመች መሆኑን ሳስብ፤ እንደቻይና ሁሉ የሺ ዘመናት ገናና ታሪክና አኩሪ ገድል ያላት ኢትዮጵያስ የሚል ተጠየቅ እንዳውጠነጥን አድርጎኛል። ቻይናዊያን የዘመን የፈተና ቋጠሮዎቻቸውን ፈታተው ከዛሬ ከፍታ ሰገነት ላይ ወጥተዋል። ከዛሬም በበለጠ ነገን በጽኑ መሰረት ላይ እየገነቡ ነው። እኛስ? ብዬ ሳስብ በቁጭትና በተስፋ ተዋጥኩ! ሰላም!