ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በምስራቅ ጎጃም ዞን በፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ሆነዋል
Apr 23, 2026 18
ደብረ ማርቆስ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ፍራፍሬዎች ልማት ሥራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጨማሪ ገቢ በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገለጹ። በዞኑ ከ20 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በቆላና ደጋ የፍራፍሬ ተክሎች እየለማ መሆኑም ተመላክቷል። በምስራቅ ጎጃም ዞን የስናን ወረዳ አርሶ አደር ጌታሁን መንግስቴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከሰብል ልማት ሥራቸው ጎን ለጎን ከስምንት ዓመት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የአፕል ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ እያደረጋቸው ነው። በአሁኑ ወቅት ከሩብ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ልማቱን እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   በየዓመቱ ከሚሰበስቡት የአፕል ምርት እስከ 30 ሺህ ብር ተጨማሪ ገቢ እያገኙ እንደሆነና ቆጥበው ተጨማሪ ሃብት ለማፍራት እንዳገዛቸው ተናግረዋል። ዘንድሮም የአፕል ምርት አያያዙ የተሻለ መሆኑን ገልጸው፣ በምርት ሽያጩ ካለፈው ዓመት የተሻለ ገቢ ለማግኘት ተግተው እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዞኑ የጎዛምን ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር የሻነህ ጓዴ በበኩላቸው እንዳሉት ከአቮካዶ፣ ማንጎ እና ሎሚ ምርት ሽያጭ በዓመት ከ50 ሺህ ብር በላይ ገቢ እያገኙ ይገኛሉ። ከሰብል ልማት ሥራቸው ጎን ለጎን እያካሄዱት ያለው የፍራፍሬ ልማት ገቢያቸውን ከማሳደጉ ባሻገር ልጆቻቸውን የተመጣጠነ ምግብ ለመመገብና ጤናማ ሆነው እንዲያድጉ እያገዛቸው መሆኑን አስረድተዋል።   በምስራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባለሙያ ተሾመ በላይ፣ በዞኑ ከ20 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የፍራፍሬ ልማት እየተከናወነና በልማቱም አርሶ አደሮች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ዘንድሮ በዞኑ ከለማው አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ብርቱካን፣ ሎሚ፣ ፓፓያ፣ አፕልና ሌሎች የቆላና የደጋ ፍራፍሬዎች እስካሁን ከ80ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቦ ለገበያ መቅረቡን ጠቁመው፣ በቀሪ ወራትም የበለጠ ምርት ይቀርባል ብለዋል። ከፍራፍሬ ልማት የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ በመጪው የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የሚተከሉ ከ818 ሺህ በላይ የፍራፍሬ ችግኞች መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት በዞኑ ከፍራፍሬ ልማት ከ278ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለገበያ መቅረቡን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በክልሉ ለተመዘገበው ልማትና መልካም አስተዳደር የምክር ቤቶች ሚና ከፍተኛ ነው
Apr 23, 2026 53
ሚዛን አማን፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለተመዘገበው ልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መጠናከር ምክር ቤቶች የላቀ ሚና እንደነበራቸው ተገለጸ ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤትና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ለ7ኛ ጊዜ የሚደረገው የጋራ የምክክር መድረክ የልምድ ልውውጥና ውጤታማ ተሞክሮዎች የሚቀመሩበት ነው ። ምክር ቤቱ ከሕዝብ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የምክር ቤቶችን አደረጃጀት በማጠናከርና የክልሉ ሕገ መንግስት ያስቀመጣቸውን ኃላፊነቶች በተገቢው መንገድ በመፈፀም ላይ ነው ብለዋል።   ከዚህ ውስጥም ባለፉት ዓመታት የአስፈጻሚ አካላት ተግባራት ላይ ክትትል፣ ድጋፍና ቁጥጥር በማድረግ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና ልማቶች በተገቢው መንገድ እንዲከናወኑ የድርሻውን መወጣቱን አስረድተዋል ። በዚህም የሕዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውን ገልጸዋል። የመንግስት የልማት ኢኒሼቲቮች የዜጎችን ኑሮን ለማሻሻል የሚያስችሉ በመሆናቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መተግበር እንዲችሉ ምክር ቤቶቹ ጥረት እያደረጉ መሆኑን አመልክተዋል።   የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ጌድዮን ኮስታብ በበኩለቸው፤ በሕዝቦች መካከል አንድነትና የእርስ በእርስ ትስስርን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የዞኑን የልማት ሥራዎች መስክ ላይ ወርዶ በመከታተልና አቅጣጫ በማሳየት መልካም ተሞክሮዎች እንዲያድጉ ምክር ቤቱ ኃላፊነቱን ያጠናክራል ብለዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የምክር ቤቶቹ የጋራ የምክክር መድረክ ላይ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤን ጨምሮ የስድስቱም ዞኖች አፈ ጉባኤዎችና ቋሚ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል።
ባህልን በአግባቡ በማልማት እና በማስተዋወቅ ለሀገር እድገት ማዋል ይገባል
Apr 23, 2026 43
ጅማ ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ነባር ባህላዊ እሴቶችን በቴክኖሎጂ ታግዞ በማልማት እና በማስተዋወቅ ለሀገር እድገት መጠቀም ወሳኝ መሆኑ ተመላከተ። በጅማ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ በሚገኘው 6ኛው ዓለም አቀፍ የኦሮሞ ጥናት ኮንፈረንስ ላይ ባህልን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለሀገር እድገት ስለማዋል ያለመ ውይይት እየተደረገ ነው።   በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ኦቱከና ኦዳ (ዶ/ር) ፤ ባህልን በመጠበቅና በመንከባከብ ለሀገር እድገት ማዋል እንደሚገባ አሳስበዋል። ባህል ቋንቋ ወይም ነባር እሴት ብቻ ሳይሆን፣ ባህልን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት ዓለም አቀፋዊ የማድረግ ስራን ይጨምራል ብለዋል። በተለይም ዘመን ተሻጋሪ ባህላዊ እሴቶችን ዘመኑን በዋጀ መልኩ በመጠበቅና ዲጂታላይዝ በማድረግ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉም ገልጸዋል። ለዚህ ስኬት ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ምሁራን የላቀ ድርሻ እንዳላቸው ጠቁመዋል።   የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባህል ለሀገር ሰላምና አንድነት ያለውን ሚና ገልጸው፣ ዩኒቨርሲቲው ባለፉት 10 ዓመታት በዚህ ዘርፍ በስፋት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው ከሌሎች 12 ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት በኦሮሞ ባህል ጥናት ላይ የጀመረው ስራ ተጨባጭ ለውጦችን እያመጣ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ የሚካሄዱ ጥናትና ምርምሮች የዜጎችን ሕይወት በሚቀይር መልኩ ወደ ህዝብ መውረድ አለባቸው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። በዚህ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ ከተለያዩ የምርምር ተቋማት የተጋበዙ ተመራማሪዎች የጥናት ጽሑፍ እያቀረቡ ሲሆን፤ አባ ገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ
Apr 23, 2026 80
‎ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከነበረው ግትር ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አስተሳሰብ ተላቃ፣ ትኩረቱን በተግባራዊ አፈጻጸም ላይ ያደረገ አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ እይታ የተቃኘ የፖሊሲ ማዕቀፍ መከተል ከጀመረች ሰነባብታለች። ‎ይኅው አዲስ አቅጣጫ፤ ሀገሪቱ ለወቅታዊ የዓለምና የሀገር ውስጥ ነባራዊ ሁኔታዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራዊ መፍትሄዎችን እንድትቀይስ አስችሏታል። በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የሪፎርም ጉዞ፣ መንግሥትንና የግሉን ዘርፍ እንደ ወሳኝ አጋር በማየት፣ በውጤትና በውጤታማነት ላይ የተገነባ አዲስ የመንግሥት የሥራ ባህልን ተቋማዊ አድርጓል። ‎‎በዚህ ገቢር ነበብ እይታ አማካኝነት፣ በሚከተሉት ስምንት ቁልፍ ምሰሶዎች ወሳኝ ስኬቶች ተመዝግበዋል፦ ‎• በኢኮኖሚ ዕይታ ረገድ፦ የመንግሥትን ሚና ዳግም በመተርጎም፣ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና ዘርፈ-ብዙ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎች አማካኝነት የገበያ ውድድር እንዲሰፍንና የኢኮኖሚ አቅም እንዲጎለብት ተደርጓል። ‎• በአማራጭ ፋይናንስ ዘርፍ፦ የካፒታል ገበያ ልማትን በማብሰር፣ የመንግሥትና የግል አጋርነትን በማጠናከር እና ዘመናዊ የገንዘብ ገበያ በመፍጠር የሀገሪቱን የፋይናንስ አማራጮች ማሳደግ ተችሏል። ‎• በኢኮኖሚ አመራር በኩል፦ በመደበኛ ክትትልና ግምገማ፣ በማክሮ ኮሚቴና በዘርፍ ካውንስሎች የተቀናጀ አሰራር አማካኝነት የገንዘብ ፖሊሲና የፕሮጀክቶች አስተዳደር ይበልጥ ውጤታማና ቀልጣፋ እንዲሆን ተደርጓል። ‎• የግል ዘርፍ ሚናን በማሳደግ፦ የግሉ ዘርፍ ከማህበራዊ ኃላፊነት ባለፈ የኢኮኖሚው መሪና ዋና ሞተር እንዲሆን በማድረግ እንደ ትልቅ የልማት አጋር እንዲሳተፍ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል። ‎• በልማት አጋርነትና ንግድ ትስስር ፦ የብድር ሽግሽግና አዲስ ፋይናንስን በማረጋገጥ፣ ለዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት የሚደረገውን ሂደት በማፋጠንና የAfCFTA ትግበራን ውጤታማ በማድረግ የሀገሪቱ ዓለም አቀፋዊ የንግድ ተወዳዳሪነት ከፍ ብሏል። ‎• በማህበራዊ ደህንነት ረገድ፦ አካታችነትን፣ ተደራሽነትንና ጥራትን መሠረት ያደረገ የሰው ተኮር ድጋፍ ሥርዓት በመዘርጋት፣ የማህበራዊ ጥበቃ አገልግሎቶች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ማድረግ ተችሏል። ‎• በፍትሃዊ የመሰረተ ልማት ስርዓት ፦ የአካባቢ ጸጋን መሠረት ያደረገ፣ በግልጽ የሕግ ማዕቀፍ የሚመራና ያለፉ የፍትሃዊነት ክፍተቶችን የሚሞላ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥርዓት ተግባራዊ ሆኗል። ‎• በስርዓት ግንባታ በኩል፦ ብሔራዊ አካታች ምክክርን በማካሄድ፣ በፍትህና በሲቪል ሰርቪስ ዘርፎች ሪፎርም በማድረግ እንዲሁም የዲሞክራሲ ተቋማትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ውጤቶች ተመዝግበዋል። #PMOEthiopia
ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 35 ባለሀብቶችን ወደ ስራ አስገብቷል
Apr 23, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ፓርኮች ኮርፖሬሽን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 35 ባለሀብቶችን ተቀብሎ ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ገለጸ። ኮርፖሬሽኑ በተለይ የገቢ ምርቶችን በሚተኩ የልማት ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራቱም ውጤታማ ጅምር መኖሩን አረጋግጧል። በኮርፖሬሽኑ የልማት ዘርፍ ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ቱፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኮርፖሬሽኑ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የማልማት ፣ የማስተዳደርና ገቢ የማመንጨት ተልዕኮውን በስኬት እየተወጣ ይገኛል። በበጀት ዓመቱም ባለሀብቶች በቡልቡላ የተቀናጀ ኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ በመካከለኛ ኢንዱስትሪ ማዕከላት፣ ጥቃቅን ኢንዱስትሪ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ገቢን ለማመንጨትና ተኪ ምርቶችን ለማምረት ወደ ስራ መግባታቸውንም ነው የገለጹት።   ባለሀብቶቹ በዋናነት በምግብ ዘይት፣ በጥራጥሬና ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በተለያዩ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ላይ መሰማራታቸውን ተናግረዋል። ባለሀብቶቹ ስራ የጀመሩት መሰረተ ልማት በተሟላላቸው ስፍራዎች መሆኑን የገለጹት አቶ ሰለሞን፣ በዋናነትም የቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና በስሩ የሚገኙ 6 መካከለኛ ኢንዱስትሪ ማዕከላት መሆናቸውን ጠቁመዋል። በበጀት ዓመቱም 35 ባለሀብቶችን ወደ ማምረት ስራ ማስገባት በመቻሉ በአጠቃላይ የአልሚ ባለሀብቶች ቁጥር 81 ደርሷል ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት በኮርፖሬሽኑ ስር በሚገኙ ፓርኮች ተመርቶ ለገበያ የቀረበ ሲሆን፣ ከዚህም 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል።   ወደ ስራ በገቡት አምራች ኢንዱስትሪዎች 3 ሺህ 225 ዜጎች የስራ ዕድል ማግኘታቸውንም አስታውቀዋል። በነቀምቴ የተቀናጀ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከለማው 60 ሄክታር መሬት ውስጥ 10 ሄክታሩ ለባለሀብቶች የተላለፈ ሲሆን ከተገነቡት ሶስት ሼዶች መካከል ሁለቱ ለባለሀብቶች እንዲተላለፉ መደረጉንም ገልፀዋል። ኮርፖሬሽኑ በቀጣይም የለሙ መሬቶችን በማቅረብና አምራቾች ምርቶቻቸውን በስፋት ለገበያ እንዲያቀርቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ምክትል ስራ አስፈጻሚው አረጋግጠዋል።
የሚታይ
አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ
Apr 23, 2026 80
‎ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከነበረው ግትር ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አስተሳሰብ ተላቃ፣ ትኩረቱን በተግባራዊ አፈጻጸም ላይ ያደረገ አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ እይታ የተቃኘ የፖሊሲ ማዕቀፍ መከተል ከጀመረች ሰነባብታለች። ‎ይኅው አዲስ አቅጣጫ፤ ሀገሪቱ ለወቅታዊ የዓለምና የሀገር ውስጥ ነባራዊ ሁኔታዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራዊ መፍትሄዎችን እንድትቀይስ አስችሏታል። በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የሪፎርም ጉዞ፣ መንግሥትንና የግሉን ዘርፍ እንደ ወሳኝ አጋር በማየት፣ በውጤትና በውጤታማነት ላይ የተገነባ አዲስ የመንግሥት የሥራ ባህልን ተቋማዊ አድርጓል። ‎‎በዚህ ገቢር ነበብ እይታ አማካኝነት፣ በሚከተሉት ስምንት ቁልፍ ምሰሶዎች ወሳኝ ስኬቶች ተመዝግበዋል፦ ‎• በኢኮኖሚ ዕይታ ረገድ፦ የመንግሥትን ሚና ዳግም በመተርጎም፣ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና ዘርፈ-ብዙ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎች አማካኝነት የገበያ ውድድር እንዲሰፍንና የኢኮኖሚ አቅም እንዲጎለብት ተደርጓል። ‎• በአማራጭ ፋይናንስ ዘርፍ፦ የካፒታል ገበያ ልማትን በማብሰር፣ የመንግሥትና የግል አጋርነትን በማጠናከር እና ዘመናዊ የገንዘብ ገበያ በመፍጠር የሀገሪቱን የፋይናንስ አማራጮች ማሳደግ ተችሏል። ‎• በኢኮኖሚ አመራር በኩል፦ በመደበኛ ክትትልና ግምገማ፣ በማክሮ ኮሚቴና በዘርፍ ካውንስሎች የተቀናጀ አሰራር አማካኝነት የገንዘብ ፖሊሲና የፕሮጀክቶች አስተዳደር ይበልጥ ውጤታማና ቀልጣፋ እንዲሆን ተደርጓል። ‎• የግል ዘርፍ ሚናን በማሳደግ፦ የግሉ ዘርፍ ከማህበራዊ ኃላፊነት ባለፈ የኢኮኖሚው መሪና ዋና ሞተር እንዲሆን በማድረግ እንደ ትልቅ የልማት አጋር እንዲሳተፍ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል። ‎• በልማት አጋርነትና ንግድ ትስስር ፦ የብድር ሽግሽግና አዲስ ፋይናንስን በማረጋገጥ፣ ለዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት የሚደረገውን ሂደት በማፋጠንና የAfCFTA ትግበራን ውጤታማ በማድረግ የሀገሪቱ ዓለም አቀፋዊ የንግድ ተወዳዳሪነት ከፍ ብሏል። ‎• በማህበራዊ ደህንነት ረገድ፦ አካታችነትን፣ ተደራሽነትንና ጥራትን መሠረት ያደረገ የሰው ተኮር ድጋፍ ሥርዓት በመዘርጋት፣ የማህበራዊ ጥበቃ አገልግሎቶች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ማድረግ ተችሏል። ‎• በፍትሃዊ የመሰረተ ልማት ስርዓት ፦ የአካባቢ ጸጋን መሠረት ያደረገ፣ በግልጽ የሕግ ማዕቀፍ የሚመራና ያለፉ የፍትሃዊነት ክፍተቶችን የሚሞላ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥርዓት ተግባራዊ ሆኗል። ‎• በስርዓት ግንባታ በኩል፦ ብሔራዊ አካታች ምክክርን በማካሄድ፣ በፍትህና በሲቪል ሰርቪስ ዘርፎች ሪፎርም በማድረግ እንዲሁም የዲሞክራሲ ተቋማትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ውጤቶች ተመዝግበዋል። #PMOEthiopia
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ዘርፍ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል ቁርጠኝነቷን ዳግም ታረጋግጣለች 
Apr 23, 2026 86
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ዘርፍ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል ቁርጠኝነቷን ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ መራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነትም እንዲሁ ዳግም ታረጋግጣለች ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን አዲስ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ጠዋት የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በውይይታችንም በተለያዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የመከርን ሲሆን፤ በተለይም በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ነው ያሉት። በዚህም ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ መራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉ ገልጸዋል። የፈጠራ ሥራዎች ለአፍሪካ ዕድገት ምንጊዜም ወሳኝ መሰረት መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ጠቁመዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ መራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ቁርጠኛ መሆኗንም ገልጸዋል። ይህንን ርዕይ ወደ ተጨባጭና አካታች ውጤት ለመለወጥ ከአፍሪካ ሲዲሲ (Africa CDC) እና በመላው አህጉሪቱ ከሚገኙ አጋሮች ጋር በቅርበት ለመሥራት ዝግጁ ነኝ ሲሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የራስን አቅም የመገንባት ታሪካዊ ጉዞ ነው 
Apr 23, 2026 100
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገርን የኢኮኖሚ ነፃነት በማረጋገጥ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ታሪካዊ ጉዞ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ። ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ይህን የተናገሩት "ድሬ ታምርት ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው የአምራች ኢንዱስትሪዎች ኤክስፖ የፓናል ውይይት ላይ ነው።   አቶ መላኩ በወቅቱም፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ በተደረገው ድጋፍና ክትትል እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በንቅናቄው የተዘጉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲመለሱ በማድረግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በጥራትና በስፋት እየተተኩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ እና የስራ ዕድል በመፍጠር ረገድም መሠረታዊ ውጤቶች መገኘታቸውን በመጥቀስ። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገርን የኢኮኖሚ ነፃነት በማረጋገጥ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ታሪካዊ ጉዞ መሆኑን በአፅንኦት ገልጸዋል። በሌሎች ሀገራት አልባሳት፣ መድኃኒት፣ መገልገያዎችና ሌሎች ምርቶች ላይ ጥገኛ የሆነ አገር ሉዓላዊነቱን ማረጋገጥ እንደማይችል በማመላከት። በንቅናቄው በተሰሩ ስራዎች በዘንድሮ በጀት ዓመት ብቻ 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ የውጭ ሀገራት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት መዘጋጀታቸውን አስታውሰዋል። ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግና በኢኮኖሚው ውስጥ የመሪነት ድርሻውን እንዲያረጋግጥ የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች እየተደረጉ ይገኛሉም ብለዋል።   የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች በተደረጉ ድጋፎች ተዘግተው የነበሩ 15 ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ማምረት በማሸጋገር ከ9 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል። አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ እና ወጪ ምርቶችን በስፋትና በጥራት እያመረቱ መሆኑን ጠቅሰው ከንቅናቄው በኋላ የኢንዱስትሪዎቹ የማምረት አቅም ከ42 በመቶ ወደ ወደ 64 በመቶ ከፍ ማለቱን አንስተዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ፤ ባለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተሰሩ ስራዎች ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻላቸውን ገልፀዋል።   በተደረጉ ሁሉን አቀፍ ድጋፎችና ክትትሎች የተዘጉ እና በግንባታ ላይ ያሉ ፋብሪካዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን በማስታወስ። ባለፉት ዓመታት 253 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ከ2 ሺህ 620 በላይ ባለሃብቶች ፍቃድ ወስደው ወደ ዘርፉ መግባታቸውን ጠቅሰው ወደ ማምረት የተሸጋገሩትም ከ10ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥረዋል ብለዋል። በፓናል ውይይቱ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ባለቤቶች፣ የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው ተሾሙ
Apr 23, 2026 151
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሹመዋል። ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች የምትገኘውን የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በተላከው የሹመት ደብዳቤ ላይ "የተከበሩ የእርስዎ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ አድርጓል" የሚል ሀሳብ መስፈሩን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። "ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል" የሚል መልዕክትም በተላከው የሹመት ደብዳቤ ላይ ሰፍሯል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር፣ ኢትዮጵያ በዲጂታላይዜሽን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች ያስመዘገበችው እድገት ከፍተኛ አፈጻጸም ማሳየቱን ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኢ-መንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል፣ በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩትን ማቋቋም እንዲሁም ሀገራዊ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ መንደፍ ለለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውንም አክሎ ገልጿል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የታቀደው ዕቅድ፤ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ተወያዩ
Apr 23, 2026 106
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። በውይይታቸውም በተለያዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል፡፡ በተለይም በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሰጣቸውን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት መነጋገራቸውን ጠቁመዋል። የፈጠራ ሥራዎች ለአፍሪካ ዕድገት ምንጊዜም ወሳኝ መሰረት ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ማረጋገጧንም ገልጸዋል። ይህንን ርዕይ ወደ ተጨባጭና አካታች ውጤት ለመለወጥ ከአፍሪካ ሲዲሲ (Africa CDC) እና በመላው አህጉሪቱ ከሚገኙ አጋሮች ጋር በቅርበት ለመሥራት ዝግጁ ነኝ ሲሉም አስፍረዋል፡፡

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በክልሉ ለተመዘገበው ልማትና መልካም አስተዳደር የምክር ቤቶች ሚና ከፍተኛ ነው
Apr 23, 2026 53
ሚዛን አማን፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለተመዘገበው ልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መጠናከር ምክር ቤቶች የላቀ ሚና እንደነበራቸው ተገለጸ ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤትና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ለ7ኛ ጊዜ የሚደረገው የጋራ የምክክር መድረክ የልምድ ልውውጥና ውጤታማ ተሞክሮዎች የሚቀመሩበት ነው ። ምክር ቤቱ ከሕዝብ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የምክር ቤቶችን አደረጃጀት በማጠናከርና የክልሉ ሕገ መንግስት ያስቀመጣቸውን ኃላፊነቶች በተገቢው መንገድ በመፈፀም ላይ ነው ብለዋል።   ከዚህ ውስጥም ባለፉት ዓመታት የአስፈጻሚ አካላት ተግባራት ላይ ክትትል፣ ድጋፍና ቁጥጥር በማድረግ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና ልማቶች በተገቢው መንገድ እንዲከናወኑ የድርሻውን መወጣቱን አስረድተዋል ። በዚህም የሕዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውን ገልጸዋል። የመንግስት የልማት ኢኒሼቲቮች የዜጎችን ኑሮን ለማሻሻል የሚያስችሉ በመሆናቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መተግበር እንዲችሉ ምክር ቤቶቹ ጥረት እያደረጉ መሆኑን አመልክተዋል።   የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ጌድዮን ኮስታብ በበኩለቸው፤ በሕዝቦች መካከል አንድነትና የእርስ በእርስ ትስስርን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የዞኑን የልማት ሥራዎች መስክ ላይ ወርዶ በመከታተልና አቅጣጫ በማሳየት መልካም ተሞክሮዎች እንዲያድጉ ምክር ቤቱ ኃላፊነቱን ያጠናክራል ብለዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የምክር ቤቶቹ የጋራ የምክክር መድረክ ላይ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤን ጨምሮ የስድስቱም ዞኖች አፈ ጉባኤዎችና ቋሚ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሪፎርም በፓርቲዎች መካከል የትብብርና የፉክክር ሚዛን ማስጠበቅ ያስቻለ ምኅዳር ፈጥሯል 
Apr 22, 2026 1357
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሪፎርም በፓርቲዎች መካከል የትብብርና የፉክክር ሚዛን ማስጠበቅ ያስቻለ ምኅዳር መፍጠሩን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። የ2018 በጀት ዓመት ሦስተኛው የመቶ ቀናት እና የዘጠኝ ወራት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።   በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በሰጡት ማብራሪያ፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች የተወሰዱ የሪፎርም እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች አስገኝተዋል ብለዋል። በዚህም በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የተወሰዱ የሪፎርም እርምጃዎች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ በመፈጸም ተጠባቂ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ገልጸዋል። ይህም የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ እመርታዊ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ ማስቻሉንም ተናግረዋል። ገዥው ፓርቲ በፖለቲካው መስክ የወሰዳቸው የሪፎርም እርምጃዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የትብብርና ፉክክር ሚዛንን ማስጠበቅ ያስቻለ ምኅዳር መፍጠሩን አስረድተዋል። በዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር የሚሰሩበትን ጤናማ የፉክክር መድረክ መፈጠሩን አንስተዋል። ገዥው ፓርቲም በየደረጃው የሥራ ኃላፊዎችን የመመደብ ሥልጣንና ኃላፊነት እንዳለው አስታውሰው፤ የትብብርና የሃሳብ ልዕልና ባህልን ለማዳበር የኢትዮጵያን የመግባባት ዴሞክራሲን ማጠናከር የሚያስችል የተሳትፎ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል። ከፌዴራል እስከ ወረዳ በሚገኙ የመንግስት መዋቅሮችም ከ275 በላይ የሚሆኑ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተመድበው ህዝባቸውንና ሀገራቸውን እያገለገሉ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሪፎርም በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትና አንድነትን ለመፍጠር አካታች ሀገራዊ ምክክሩ የተሻለ የምክክር ምዕራፍ ላይ መድረሱንም ጠቁመዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሪፎርም ውጤታማነትን በማስቀጠል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የተጀመሩ ጥረቶች የበለጠ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አቶ አደም አረጋግጠዋል። መንግስትና ገዥው ፓርቲም መርህን በጠበቀ መልኩ ሀገራዊ ምክክሩ በህዝብና ባለድርሻ አካላት የላቀ ተሳትፎ ግቡን እንዲመታ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።   በሌላ መልኩ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሌሎች ሀገራት በአርዓያነት የሚወስዱት ተጨባጭ ውጤቶች እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም የኢትዮጵያ ብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የሀገር ውስጥ ፍጆታን በማሟላት የዓለም አቀፍ ወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ የሚያስችል ስኬት ማስገኘቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት እንዲመረት እና የተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በማሳደግ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ እመርታዊ ውጤት ማስገኘቱን ጠቅሰዋል። በማህበራዊ ዘርፍም ፍትሕዊ የመሰረተ ልማት ተደራሽነቶች ጥራትና አካታችነትን በማስጠበቅ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደጉን አስገንዝበዋል። በተለይም የትምህርት ለትውልድ መርሃ ግብር የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት የትምህርት ጥራትን የሚያስጠብቅ ውጤት እየተገኘበት መሆኑን አስታውቀዋል። በአጠቃላይ በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ክብር በማስጠበቅ ሁለንተናዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ የልማት ድሎች መገኘታቸውን አብራርተዋል። በቀጣይም የመንግስት፣ የግሉ ዘርፍና የህዝብን ተሳትፎና አቅሞችን በመደመር ሁለንተናዊ ብልፅግና፣ የዳበረ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር የሰፈነባት፣ ዘላቂና አዎንታዊ ሰላም ባለቤት ኢትዮጵያን መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል።
የኢትዮጵያን የተጽዕኖና የትብብር አድማስ ያሳደጉ ስትራቴጂካዊ የዲፕሎማሲ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Apr 22, 2026 738
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያን የተጽዕኖና የትብብር አድማስ ያሳደጉ ስትራቴጂካዊ የዲፕሎማሲ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለፁ። በኢኮኖሚ፣ በተቋም ግንባታና በአካባቢ የተከናወኑ ተግባራትም ለኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ስኬት የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የ2018 በጀት ዓመት ሦስተኛው የመቶ ቀናት እና የዘጠኝ ወራት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) በዲፕሎማሲ መስክ የተገኙ ውጤቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት አበረታች የዲፕሎማሲ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላት ተጽዕኖ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን አስታወቀዋል። የኢትዮጵያን አንኳር ስትራቴጂካዊ ፍላጎት የሆነው የባህር በር አጀንዳ በዓለም አቀፍ መድረኮችና በሁለትዮሽ ግንኙነቶች ትልቅ ትኩረት እንዲያገኝ ተደርጓል ብለዋል። ይህም የተለያዩ አካላት የኢትዮጵያን ጥያቄ እንዲገነዘቡና ለጉዳዩ በጋራ መፍትሔ መፈለግ አስፈላጊ መሆኑን እንዲረዱ በማድረግ ረገድ ትልቅ ድል መገኘቱን ገልጸዋል። ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ጫናዎች ቢኖሩም፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና ህዝብ ጫናዎቹን በመቋቋም የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ እንዲገባ ማድረግ መቻሉ ሌላኛው ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የብሪክስ ሙሉ አባል ሀገር ሆና መመረጧና ንቁ ተሳትፎ መጀመሯ የሀገሪቱን ዓለም አቀፍ ተቀባይነት የሚያሳይ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንትና ለኢኮኖሚ አጋርነት ያላት ተፈላጊነት እየጨመረ መምጣቱንም ጠቅሰዋል።   የቅርብና የሩቅ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙም አስረድተዋል። የከፍተኛ አመራሮች የጉብኝት ልውውጦችና የሚፈረሙ ስምምነቶች የኢትዮጵያ የትብብር አድማስ መስፋቱን የሚያሳዩ ተጨባጭ ውጤቶች ናቸው ብለዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የውሳኔ ሰጪ ተቋማት ውስጥ በከፍተኛ ድምፅ ስትመረጥ መቆየቷን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በተለይም በግለሰብ ደረጃ የሚወከሉ የኢትዮጵያ እጩዎች በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ መሆናቸው የሀገሪቱ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እያደገ መምጣቱን የሚያረጋግጥ እንደሆነ ገልፀዋል። የዲፕሎማሲ ስኬቱ በተጨባጭ የሀገር ውስጥ ስራዎች ላይ የተመሰረተ መሆኑንም አብራርተዋል። የኢኮኖሚ ሪፎርሙ የሀገሪቱን ተቋማት በማጠናከር ለውጤት የበቁ አቅሞች እንዲሆኑ ማስቻሉንም አንስተዋል። በአካባቢ ጥበቃና በታዳሽ ኃይል ኢንቨስትመንት የተሰሩ ስራዎች ለሌሎች ሀገራት እንደ ተምሳሌት እየታዩ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። የከተማና የገጠር ልማት እንቅስቃሴዎች ተደምረው ኢትዮጵያ ለትብብርና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንድትሆን አድርገዋታል ብለዋል። በኢኮኖሚ፣ በተቋም ግንባታና በአካባቢ ጥበቃ የተከናወኑ ተግባራት ለኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ስኬት የጀርባ አጥንት መሆናቸውንም ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።
በያዝነው ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም የምርጫውን ዕለት እየጠበቅን ነው
Apr 22, 2026 728
ሀዋሳ/ቦንጋ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በያዝነው ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም የምርጫውን ዕለት እየጠበቅን እንገኛለን ሲሉ የሀዋሳና የቦንጋ ከተሞች ነዋሪዎች ገለጹ። በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቃል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሃዋሳና የቦንጋ ከተሞች ነዋሪዎች ፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በያዝነው ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም የምርጫውን ዕለት እየጠበቅን እንገኛለን ብለዋል። አቶ አሸናፊ አለሙ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ፣ የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣትና ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ በመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡   ምርጫ ቦርድ ያመቻቸው ተጨማሪ የምዝገባ ቀን በስራ መደራረብ ምክንያት ጊዜ ላላገኙ ዜጎች መልካም እድልን የፈጠረ በመሆኑ ካርድ ለመውሰድ አስችሎኛል ነው ያሉት፡፡ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ ለመሆን የምርጫ ካርድ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን በማመን በመጨረሻው ቀን ካርድ ወስጃለሁ የሚሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ አቶ ታረቀኝ ድቃሶ ናቸው፡፡   ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ለሀገር የሚጠቅም ፓርቲን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረው የፓርቲዎቹን የምረጡኝ ቅስቀሳ እየተከታተሉ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ ሙሴ ኤልያስ በበኩላቸው፤ በተመቻቸላቸው ቀን ተጠቅመው የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረው ለሀገር ልማት ይጠቅማል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው ፤ለጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ካርድ በመያዝ ድምጽ የመስጫ ቀኑን እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።   በከተማው 03 ሸታ ምርጫ ጣቢያ ካርድ ሲወስዱ ያነጋገርናቸው የቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ ተማሪዎች መቅደስ መኮንን እና መሠለች ወንድሙ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። በመጨረሻ ቀንም ቢሆን ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ካርድ በመውሰዳቸው መደሰታቸውን ጠቁመው፣ ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።   ተማሪ ምናሉሽ አቱሞና ሰለሞን ኮያ በበኩላቸው በወሰዱት ካርድ ለሀገር ሰላምና ልማት ይበጃል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። ሌላው የቦንጋ ከተማ ነዋሪ አቶ አብዱልቃድር አደም በበኩላቸው፤ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ቦርዱ ለመራጮች ምዝገባ ያስቀመጠው ጊዜ ከመጠናቀቁ በፊት የምርጫ ካርድ እየወሰድን ነው
Apr 22, 2026 472
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው ቀነ ገደብ መሠረት የመራጮች ምዝገባ ከመጠናቀቁ በፊት ዛሬ የምርጫ ካርዳችንን እየወሰድን ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ሲሆን፤ እስከ ዛሬ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የተራዘመው የጊዜ ገደብ በተለያየ ምክንያት ምርጫ ካርድ ያላወጡ ዜጎች እንዲመዘገቡ መልካም አጋጣሚን ፈጥሯል። ኢዜአ በመዲናዋ ተዘዋውሮ በምርጫ ጣቢያዎች ባደረገው ቅኝት የመጨረሻዋን ቀን በመጠቀም ዜጎች ካርድ እየወሰዱ መሆኑን ተመልክቷል። በመዲናዋ በተለያዩ የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎች ተዘዋውሮ ካርዳቸውን ሲወስዱ ያገኛቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የምርጫ ካርድ ማውጣታችን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ያስችለናል ብለዋል። የምርጫ ካርድ ሲያወጣ ያገኘነው ዘሪሁን ፍቃዱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች በቂ ጊዜ ለመስጠት የምዝገባ ጊዜውን በማራዘሙ ዛሬ የድምፅ መስጫ ካርድ መውሰዱን ተናግሯል፡፡ ማርሸት ጠንክር የተባለች አስተያየት ሰጪ በበኩሏ፤ የወሰደችውን የምርጫ ካርድ በመጠቀም ግንቦት 24 በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀኛል የምትለውን እጩ ለመምረጥ መዘጋጀቷን ገልጻለች፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪ አቤል ኃይሉ በበኩሉ መምረጥ የሚያስችለኝን የመራጭነት ካርድ ወስጃለሁ ብሏል። ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገርና በተለይም ለወጣቶች ተጠቃሚነት የተሻለ ፖሊሲ ያቀረበውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቱን የተናገረው ደግሞ ካሳሁን ጉልማ የተባለ አስተያየት ሰጪ ነው።
የመራጮች ምዝገባ ቀን መራዘሙ በምርጫው እንድንሳተፍ ተጨማሪ እድል ፈጥሮልናል
Apr 22, 2026 478
ደብረ ብርሃን ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- የመራጮች ምዝገባ ቀን መራዘሙ በምርጫው እንድንሳተፍ ተጨማሪ እድል ፈጥሮልናል ሲሉ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በደብረ ብርሃን ከተማ በተለያዩ ምክንያቶች የምርጫ ካርድ ሳይወስዱ የቆዩ ነዋሪዎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ቦርዱ ለመራጮች ምዝገባ ቀን ያስቀመጠውን የጊዜ ሰሌዳ ማራዘሙ በሀገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ለማድረግ ሁኔታዎችን ያመቻቸ ነው ብለዋል። የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ በመመዝገብ ላይ የነበሩት የ65 ዓመት የእድሜ ባለፀጋ የሆኑት ወይዘሮ ጥሩነሽ ገብረወልድ ተጨማሪ የመራጮች ምዝገባ ቀናት እንዲኖር መደረጉ በምርጫው ተሳትፎ ለማድረግ እንድንችል አድርጓል ብለዋል ።   በምርጫው ይጠቅመኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅትም በምርጫው የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉት የምረጡኝ ቅስቀሳ በእውቀት ላይ ተመስርተን ለምርጫው እንድንዘጋጅ አድርጎናል ብለዋል። የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት አንዋር ደረጀ እና ወይዘሮ ሰላም ሹመት ፤በተለያዩ ምክንያቶች የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ሳይችሉ የቆዩ ቢሆንም በዛሬው እለት በተሰጣቸው የመጨረሻ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡   የመራጮች ምዝገባ ቀን መራዘሙ በምርጫው በመሳተፍ ለሀገር ሰላም ልማትና እድገት የሚጠቅም ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት እንድንዘጋጅ አድርጎናል ነው የሚሉት። ወይዘሮ ጽጌ ታየ በበኩላቸው በመጨረሻው የምዝገባ ቀን የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በጥንቃቄ በማስቀመጥ መብቴንና ጥቅሜን ያስጠብቅልኛል የሚሉትን ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት እንደሚጠቀሙበትም ነው ያነሱት። ካርድ ያላወጡ ዜጎች በዛሬው እለት በሚካሔደው የመጨረሻው የመራጮች ምዝገባ ቀን ተጠቅመው የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት መዘጋጀት እንዳለባቸውም ነው አስተያየት ሰጪዎቹ የተናገሩት።
የመመዝገቢያ ቀን መራዘሙን ተጠቅመን የምርጫ ካርድ ወስደናል- የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች   
Apr 22, 2026 460
ወላይታ ሶዶ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- የመመዝገቢያ ቀን መራዘሙን ተጠቅመው የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ያራዘመው የመራጮች ምዝገባ ቀነ ገደብ ዛሬ ይጠናቀቃል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች የመራጮች ምዝገባ ቀን መራዘሙ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም የሚበጃቸውን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን እድል የፈጠረላቸው መሆኑን ተናግረዋል ። በዚህም ዘግይተውም ቢሆን በዘንድሮው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፈው መምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል።   የከተማው ነዋሪ አቶ አብነት ኤልያስ፤ በስራ ምክንያት ካርድ ሳይወስዱ መቆየታቸውን ጠቁመው ጊዜው ሳይጠናቀቅ የመምረጥ መብታቸውን ለመጠቀም ካርድ መውሰድ በመቻላቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ቦርድ ባመቻቸው ተጨማሪ ቀን በወሰዱት የመራጭነት ካርድ የመምረጥ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን አመልክተዋል። የምርጫ ካርድ በመውሰድ መብቴን ለመጠቀም ስጠባበቅ ቆይችያለሁ ያለችው ደግሞ ወጣት ቤዛ አዲላ ናት።   የመምረጥ ዲሞክራሲያዊ መብት የሚወሰነው በምርጫ ካርድ ብቻ በመሆኑ ጊዜው ሳይጠናቀቅ ካርድ በመውሰዴ ዕድለኛ ነኝ ብላለች። የምርጫ ሂደቱ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የዜግነት ግዴታዋን እንደምትወጣም አስረድታለች። ወጣት ታምራት ደስታ በበኩሉ ተጨማሪ ቀኑን በመጠቀም ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ መውሰዱን ገልጿል።   በካርዱ ለሀገር ልማትና ዕድገት ይበጃል ያለውን ፓርቲ የመምረጥ መብቱን እንደሚጠቀምም ነው የገለጸው፡፡ በምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
ፖለቲካ
በክልሉ ለተመዘገበው ልማትና መልካም አስተዳደር የምክር ቤቶች ሚና ከፍተኛ ነው
Apr 23, 2026 53
ሚዛን አማን፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለተመዘገበው ልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መጠናከር ምክር ቤቶች የላቀ ሚና እንደነበራቸው ተገለጸ ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤትና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ለ7ኛ ጊዜ የሚደረገው የጋራ የምክክር መድረክ የልምድ ልውውጥና ውጤታማ ተሞክሮዎች የሚቀመሩበት ነው ። ምክር ቤቱ ከሕዝብ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የምክር ቤቶችን አደረጃጀት በማጠናከርና የክልሉ ሕገ መንግስት ያስቀመጣቸውን ኃላፊነቶች በተገቢው መንገድ በመፈፀም ላይ ነው ብለዋል።   ከዚህ ውስጥም ባለፉት ዓመታት የአስፈጻሚ አካላት ተግባራት ላይ ክትትል፣ ድጋፍና ቁጥጥር በማድረግ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና ልማቶች በተገቢው መንገድ እንዲከናወኑ የድርሻውን መወጣቱን አስረድተዋል ። በዚህም የሕዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውን ገልጸዋል። የመንግስት የልማት ኢኒሼቲቮች የዜጎችን ኑሮን ለማሻሻል የሚያስችሉ በመሆናቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መተግበር እንዲችሉ ምክር ቤቶቹ ጥረት እያደረጉ መሆኑን አመልክተዋል።   የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ጌድዮን ኮስታብ በበኩለቸው፤ በሕዝቦች መካከል አንድነትና የእርስ በእርስ ትስስርን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የዞኑን የልማት ሥራዎች መስክ ላይ ወርዶ በመከታተልና አቅጣጫ በማሳየት መልካም ተሞክሮዎች እንዲያድጉ ምክር ቤቱ ኃላፊነቱን ያጠናክራል ብለዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የምክር ቤቶቹ የጋራ የምክክር መድረክ ላይ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤን ጨምሮ የስድስቱም ዞኖች አፈ ጉባኤዎችና ቋሚ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሪፎርም በፓርቲዎች መካከል የትብብርና የፉክክር ሚዛን ማስጠበቅ ያስቻለ ምኅዳር ፈጥሯል 
Apr 22, 2026 1357
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሪፎርም በፓርቲዎች መካከል የትብብርና የፉክክር ሚዛን ማስጠበቅ ያስቻለ ምኅዳር መፍጠሩን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። የ2018 በጀት ዓመት ሦስተኛው የመቶ ቀናት እና የዘጠኝ ወራት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።   በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በሰጡት ማብራሪያ፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች የተወሰዱ የሪፎርም እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች አስገኝተዋል ብለዋል። በዚህም በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የተወሰዱ የሪፎርም እርምጃዎች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ በመፈጸም ተጠባቂ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ገልጸዋል። ይህም የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ እመርታዊ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ ማስቻሉንም ተናግረዋል። ገዥው ፓርቲ በፖለቲካው መስክ የወሰዳቸው የሪፎርም እርምጃዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የትብብርና ፉክክር ሚዛንን ማስጠበቅ ያስቻለ ምኅዳር መፍጠሩን አስረድተዋል። በዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር የሚሰሩበትን ጤናማ የፉክክር መድረክ መፈጠሩን አንስተዋል። ገዥው ፓርቲም በየደረጃው የሥራ ኃላፊዎችን የመመደብ ሥልጣንና ኃላፊነት እንዳለው አስታውሰው፤ የትብብርና የሃሳብ ልዕልና ባህልን ለማዳበር የኢትዮጵያን የመግባባት ዴሞክራሲን ማጠናከር የሚያስችል የተሳትፎ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል። ከፌዴራል እስከ ወረዳ በሚገኙ የመንግስት መዋቅሮችም ከ275 በላይ የሚሆኑ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተመድበው ህዝባቸውንና ሀገራቸውን እያገለገሉ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሪፎርም በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትና አንድነትን ለመፍጠር አካታች ሀገራዊ ምክክሩ የተሻለ የምክክር ምዕራፍ ላይ መድረሱንም ጠቁመዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሪፎርም ውጤታማነትን በማስቀጠል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የተጀመሩ ጥረቶች የበለጠ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አቶ አደም አረጋግጠዋል። መንግስትና ገዥው ፓርቲም መርህን በጠበቀ መልኩ ሀገራዊ ምክክሩ በህዝብና ባለድርሻ አካላት የላቀ ተሳትፎ ግቡን እንዲመታ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።   በሌላ መልኩ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሌሎች ሀገራት በአርዓያነት የሚወስዱት ተጨባጭ ውጤቶች እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም የኢትዮጵያ ብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የሀገር ውስጥ ፍጆታን በማሟላት የዓለም አቀፍ ወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ የሚያስችል ስኬት ማስገኘቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት እንዲመረት እና የተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በማሳደግ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ እመርታዊ ውጤት ማስገኘቱን ጠቅሰዋል። በማህበራዊ ዘርፍም ፍትሕዊ የመሰረተ ልማት ተደራሽነቶች ጥራትና አካታችነትን በማስጠበቅ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደጉን አስገንዝበዋል። በተለይም የትምህርት ለትውልድ መርሃ ግብር የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት የትምህርት ጥራትን የሚያስጠብቅ ውጤት እየተገኘበት መሆኑን አስታውቀዋል። በአጠቃላይ በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ክብር በማስጠበቅ ሁለንተናዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ የልማት ድሎች መገኘታቸውን አብራርተዋል። በቀጣይም የመንግስት፣ የግሉ ዘርፍና የህዝብን ተሳትፎና አቅሞችን በመደመር ሁለንተናዊ ብልፅግና፣ የዳበረ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር የሰፈነባት፣ ዘላቂና አዎንታዊ ሰላም ባለቤት ኢትዮጵያን መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል።
የኢትዮጵያን የተጽዕኖና የትብብር አድማስ ያሳደጉ ስትራቴጂካዊ የዲፕሎማሲ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Apr 22, 2026 738
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያን የተጽዕኖና የትብብር አድማስ ያሳደጉ ስትራቴጂካዊ የዲፕሎማሲ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለፁ። በኢኮኖሚ፣ በተቋም ግንባታና በአካባቢ የተከናወኑ ተግባራትም ለኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ስኬት የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የ2018 በጀት ዓመት ሦስተኛው የመቶ ቀናት እና የዘጠኝ ወራት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) በዲፕሎማሲ መስክ የተገኙ ውጤቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት አበረታች የዲፕሎማሲ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላት ተጽዕኖ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን አስታወቀዋል። የኢትዮጵያን አንኳር ስትራቴጂካዊ ፍላጎት የሆነው የባህር በር አጀንዳ በዓለም አቀፍ መድረኮችና በሁለትዮሽ ግንኙነቶች ትልቅ ትኩረት እንዲያገኝ ተደርጓል ብለዋል። ይህም የተለያዩ አካላት የኢትዮጵያን ጥያቄ እንዲገነዘቡና ለጉዳዩ በጋራ መፍትሔ መፈለግ አስፈላጊ መሆኑን እንዲረዱ በማድረግ ረገድ ትልቅ ድል መገኘቱን ገልጸዋል። ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ጫናዎች ቢኖሩም፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና ህዝብ ጫናዎቹን በመቋቋም የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ እንዲገባ ማድረግ መቻሉ ሌላኛው ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የብሪክስ ሙሉ አባል ሀገር ሆና መመረጧና ንቁ ተሳትፎ መጀመሯ የሀገሪቱን ዓለም አቀፍ ተቀባይነት የሚያሳይ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንትና ለኢኮኖሚ አጋርነት ያላት ተፈላጊነት እየጨመረ መምጣቱንም ጠቅሰዋል።   የቅርብና የሩቅ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙም አስረድተዋል። የከፍተኛ አመራሮች የጉብኝት ልውውጦችና የሚፈረሙ ስምምነቶች የኢትዮጵያ የትብብር አድማስ መስፋቱን የሚያሳዩ ተጨባጭ ውጤቶች ናቸው ብለዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የውሳኔ ሰጪ ተቋማት ውስጥ በከፍተኛ ድምፅ ስትመረጥ መቆየቷን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በተለይም በግለሰብ ደረጃ የሚወከሉ የኢትዮጵያ እጩዎች በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ መሆናቸው የሀገሪቱ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እያደገ መምጣቱን የሚያረጋግጥ እንደሆነ ገልፀዋል። የዲፕሎማሲ ስኬቱ በተጨባጭ የሀገር ውስጥ ስራዎች ላይ የተመሰረተ መሆኑንም አብራርተዋል። የኢኮኖሚ ሪፎርሙ የሀገሪቱን ተቋማት በማጠናከር ለውጤት የበቁ አቅሞች እንዲሆኑ ማስቻሉንም አንስተዋል። በአካባቢ ጥበቃና በታዳሽ ኃይል ኢንቨስትመንት የተሰሩ ስራዎች ለሌሎች ሀገራት እንደ ተምሳሌት እየታዩ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። የከተማና የገጠር ልማት እንቅስቃሴዎች ተደምረው ኢትዮጵያ ለትብብርና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንድትሆን አድርገዋታል ብለዋል። በኢኮኖሚ፣ በተቋም ግንባታና በአካባቢ ጥበቃ የተከናወኑ ተግባራት ለኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ስኬት የጀርባ አጥንት መሆናቸውንም ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።
በያዝነው ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም የምርጫውን ዕለት እየጠበቅን ነው
Apr 22, 2026 728
ሀዋሳ/ቦንጋ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በያዝነው ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም የምርጫውን ዕለት እየጠበቅን እንገኛለን ሲሉ የሀዋሳና የቦንጋ ከተሞች ነዋሪዎች ገለጹ። በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቃል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሃዋሳና የቦንጋ ከተሞች ነዋሪዎች ፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በያዝነው ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም የምርጫውን ዕለት እየጠበቅን እንገኛለን ብለዋል። አቶ አሸናፊ አለሙ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ፣ የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣትና ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ በመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡   ምርጫ ቦርድ ያመቻቸው ተጨማሪ የምዝገባ ቀን በስራ መደራረብ ምክንያት ጊዜ ላላገኙ ዜጎች መልካም እድልን የፈጠረ በመሆኑ ካርድ ለመውሰድ አስችሎኛል ነው ያሉት፡፡ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ ለመሆን የምርጫ ካርድ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን በማመን በመጨረሻው ቀን ካርድ ወስጃለሁ የሚሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ አቶ ታረቀኝ ድቃሶ ናቸው፡፡   ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ለሀገር የሚጠቅም ፓርቲን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረው የፓርቲዎቹን የምረጡኝ ቅስቀሳ እየተከታተሉ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ ሙሴ ኤልያስ በበኩላቸው፤ በተመቻቸላቸው ቀን ተጠቅመው የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረው ለሀገር ልማት ይጠቅማል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው ፤ለጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ካርድ በመያዝ ድምጽ የመስጫ ቀኑን እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።   በከተማው 03 ሸታ ምርጫ ጣቢያ ካርድ ሲወስዱ ያነጋገርናቸው የቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ ተማሪዎች መቅደስ መኮንን እና መሠለች ወንድሙ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። በመጨረሻ ቀንም ቢሆን ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ካርድ በመውሰዳቸው መደሰታቸውን ጠቁመው፣ ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።   ተማሪ ምናሉሽ አቱሞና ሰለሞን ኮያ በበኩላቸው በወሰዱት ካርድ ለሀገር ሰላምና ልማት ይበጃል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። ሌላው የቦንጋ ከተማ ነዋሪ አቶ አብዱልቃድር አደም በበኩላቸው፤ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ቦርዱ ለመራጮች ምዝገባ ያስቀመጠው ጊዜ ከመጠናቀቁ በፊት የምርጫ ካርድ እየወሰድን ነው
Apr 22, 2026 472
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው ቀነ ገደብ መሠረት የመራጮች ምዝገባ ከመጠናቀቁ በፊት ዛሬ የምርጫ ካርዳችንን እየወሰድን ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ሲሆን፤ እስከ ዛሬ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የተራዘመው የጊዜ ገደብ በተለያየ ምክንያት ምርጫ ካርድ ያላወጡ ዜጎች እንዲመዘገቡ መልካም አጋጣሚን ፈጥሯል። ኢዜአ በመዲናዋ ተዘዋውሮ በምርጫ ጣቢያዎች ባደረገው ቅኝት የመጨረሻዋን ቀን በመጠቀም ዜጎች ካርድ እየወሰዱ መሆኑን ተመልክቷል። በመዲናዋ በተለያዩ የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎች ተዘዋውሮ ካርዳቸውን ሲወስዱ ያገኛቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የምርጫ ካርድ ማውጣታችን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ያስችለናል ብለዋል። የምርጫ ካርድ ሲያወጣ ያገኘነው ዘሪሁን ፍቃዱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች በቂ ጊዜ ለመስጠት የምዝገባ ጊዜውን በማራዘሙ ዛሬ የድምፅ መስጫ ካርድ መውሰዱን ተናግሯል፡፡ ማርሸት ጠንክር የተባለች አስተያየት ሰጪ በበኩሏ፤ የወሰደችውን የምርጫ ካርድ በመጠቀም ግንቦት 24 በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀኛል የምትለውን እጩ ለመምረጥ መዘጋጀቷን ገልጻለች፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪ አቤል ኃይሉ በበኩሉ መምረጥ የሚያስችለኝን የመራጭነት ካርድ ወስጃለሁ ብሏል። ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገርና በተለይም ለወጣቶች ተጠቃሚነት የተሻለ ፖሊሲ ያቀረበውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቱን የተናገረው ደግሞ ካሳሁን ጉልማ የተባለ አስተያየት ሰጪ ነው።
የመራጮች ምዝገባ ቀን መራዘሙ በምርጫው እንድንሳተፍ ተጨማሪ እድል ፈጥሮልናል
Apr 22, 2026 478
ደብረ ብርሃን ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- የመራጮች ምዝገባ ቀን መራዘሙ በምርጫው እንድንሳተፍ ተጨማሪ እድል ፈጥሮልናል ሲሉ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በደብረ ብርሃን ከተማ በተለያዩ ምክንያቶች የምርጫ ካርድ ሳይወስዱ የቆዩ ነዋሪዎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ቦርዱ ለመራጮች ምዝገባ ቀን ያስቀመጠውን የጊዜ ሰሌዳ ማራዘሙ በሀገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ለማድረግ ሁኔታዎችን ያመቻቸ ነው ብለዋል። የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ በመመዝገብ ላይ የነበሩት የ65 ዓመት የእድሜ ባለፀጋ የሆኑት ወይዘሮ ጥሩነሽ ገብረወልድ ተጨማሪ የመራጮች ምዝገባ ቀናት እንዲኖር መደረጉ በምርጫው ተሳትፎ ለማድረግ እንድንችል አድርጓል ብለዋል ።   በምርጫው ይጠቅመኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅትም በምርጫው የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉት የምረጡኝ ቅስቀሳ በእውቀት ላይ ተመስርተን ለምርጫው እንድንዘጋጅ አድርጎናል ብለዋል። የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት አንዋር ደረጀ እና ወይዘሮ ሰላም ሹመት ፤በተለያዩ ምክንያቶች የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ሳይችሉ የቆዩ ቢሆንም በዛሬው እለት በተሰጣቸው የመጨረሻ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡   የመራጮች ምዝገባ ቀን መራዘሙ በምርጫው በመሳተፍ ለሀገር ሰላም ልማትና እድገት የሚጠቅም ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት እንድንዘጋጅ አድርጎናል ነው የሚሉት። ወይዘሮ ጽጌ ታየ በበኩላቸው በመጨረሻው የምዝገባ ቀን የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በጥንቃቄ በማስቀመጥ መብቴንና ጥቅሜን ያስጠብቅልኛል የሚሉትን ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት እንደሚጠቀሙበትም ነው ያነሱት። ካርድ ያላወጡ ዜጎች በዛሬው እለት በሚካሔደው የመጨረሻው የመራጮች ምዝገባ ቀን ተጠቅመው የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት መዘጋጀት እንዳለባቸውም ነው አስተያየት ሰጪዎቹ የተናገሩት።
የመመዝገቢያ ቀን መራዘሙን ተጠቅመን የምርጫ ካርድ ወስደናል- የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች   
Apr 22, 2026 460
ወላይታ ሶዶ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- የመመዝገቢያ ቀን መራዘሙን ተጠቅመው የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ያራዘመው የመራጮች ምዝገባ ቀነ ገደብ ዛሬ ይጠናቀቃል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች የመራጮች ምዝገባ ቀን መራዘሙ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም የሚበጃቸውን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን እድል የፈጠረላቸው መሆኑን ተናግረዋል ። በዚህም ዘግይተውም ቢሆን በዘንድሮው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፈው መምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል።   የከተማው ነዋሪ አቶ አብነት ኤልያስ፤ በስራ ምክንያት ካርድ ሳይወስዱ መቆየታቸውን ጠቁመው ጊዜው ሳይጠናቀቅ የመምረጥ መብታቸውን ለመጠቀም ካርድ መውሰድ በመቻላቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ቦርድ ባመቻቸው ተጨማሪ ቀን በወሰዱት የመራጭነት ካርድ የመምረጥ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን አመልክተዋል። የምርጫ ካርድ በመውሰድ መብቴን ለመጠቀም ስጠባበቅ ቆይችያለሁ ያለችው ደግሞ ወጣት ቤዛ አዲላ ናት።   የመምረጥ ዲሞክራሲያዊ መብት የሚወሰነው በምርጫ ካርድ ብቻ በመሆኑ ጊዜው ሳይጠናቀቅ ካርድ በመውሰዴ ዕድለኛ ነኝ ብላለች። የምርጫ ሂደቱ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የዜግነት ግዴታዋን እንደምትወጣም አስረድታለች። ወጣት ታምራት ደስታ በበኩሉ ተጨማሪ ቀኑን በመጠቀም ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ መውሰዱን ገልጿል።   በካርዱ ለሀገር ልማትና ዕድገት ይበጃል ያለውን ፓርቲ የመምረጥ መብቱን እንደሚጠቀምም ነው የገለጸው፡፡ በምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
ማህበራዊ
ባህልን በአግባቡ በማልማት እና በማስተዋወቅ ለሀገር እድገት ማዋል ይገባል
Apr 23, 2026 43
ጅማ ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ነባር ባህላዊ እሴቶችን በቴክኖሎጂ ታግዞ በማልማት እና በማስተዋወቅ ለሀገር እድገት መጠቀም ወሳኝ መሆኑ ተመላከተ። በጅማ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ በሚገኘው 6ኛው ዓለም አቀፍ የኦሮሞ ጥናት ኮንፈረንስ ላይ ባህልን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለሀገር እድገት ስለማዋል ያለመ ውይይት እየተደረገ ነው።   በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ኦቱከና ኦዳ (ዶ/ር) ፤ ባህልን በመጠበቅና በመንከባከብ ለሀገር እድገት ማዋል እንደሚገባ አሳስበዋል። ባህል ቋንቋ ወይም ነባር እሴት ብቻ ሳይሆን፣ ባህልን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት ዓለም አቀፋዊ የማድረግ ስራን ይጨምራል ብለዋል። በተለይም ዘመን ተሻጋሪ ባህላዊ እሴቶችን ዘመኑን በዋጀ መልኩ በመጠበቅና ዲጂታላይዝ በማድረግ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉም ገልጸዋል። ለዚህ ስኬት ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ምሁራን የላቀ ድርሻ እንዳላቸው ጠቁመዋል።   የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባህል ለሀገር ሰላምና አንድነት ያለውን ሚና ገልጸው፣ ዩኒቨርሲቲው ባለፉት 10 ዓመታት በዚህ ዘርፍ በስፋት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው ከሌሎች 12 ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት በኦሮሞ ባህል ጥናት ላይ የጀመረው ስራ ተጨባጭ ለውጦችን እያመጣ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ የሚካሄዱ ጥናትና ምርምሮች የዜጎችን ሕይወት በሚቀይር መልኩ ወደ ህዝብ መውረድ አለባቸው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። በዚህ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ ከተለያዩ የምርምር ተቋማት የተጋበዙ ተመራማሪዎች የጥናት ጽሑፍ እያቀረቡ ሲሆን፤ አባ ገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለአቅመ ደካሞች ያስገነባቸውን መኖሪያ ቤቶች አስረከበ
Apr 23, 2026 64
ወረር አዳብቶሌ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአፋር ክልል በተለያዩ ከተሞች ለአቅመ ደካማ ወገኖች ያስገነባቸውን መኖሪያ ቤቶች አስረከበ። ዛሬ የተረከቡት መኖሪያ ቤቶች በክልሉ ወረር አዳብቶሌ፣ ዱብቲ እና አዋሽ ከተሞች የተገነቡ 16 መኖሪያ ቤቶች ናቸው። በቤቶቹ ርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ፤ማኀበራዊ ሀላፊነትን በትብብር መወጣት መቻል የሚያስመሰግንና መጠናከር ያለበት መሆኑን ተናግረዋል።   ከሁሉ በላይ አቅመ ደካሞችን በማገዝ አብሮነትን ማሳየት የሚያስደስት ተግባር መሆኑን ገልጸው፣ ይህን በጎ ተግባር ላከናወነው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሚኒስቴሩ የበጎነት አሻራን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች እያሳረፈ መሆኑን ተናግረዋል።   ወረር አዳብቶሌ፣ ዱብቲ እና አዋሽ ከተሞችም ባለፈው የክረምት ወራት ግንባታቸው የተጀመሩ 16 የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶችን በዛሬው እለት ማስረከቡን ተናግረዋል። እርስ በርስ የመተጋገዝ ባህልን ለማስቀጠል በተለያየ ችግር ውስጥ ላሉ አቅመ ደካሞች ደረጃውን የጠበቀ መኖሪያ ቤት መገንባቱን ገልጸው፣ ለቤቶቹ ግንባታ 62 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል ብለዋል። ሚኒስቴሩ በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ የጀመረውን የበጎ አገልግሎት ሥራ ባለፈው ዓመት በኦሮሚያ ክልል ሞጆና ዱከም ከተሞች ማስቀጠሉንም አስታውሰዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር ውጤት እየተገኘበት መሆኑንም አመልክተዋል። የወረር አዳብቶሌ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አብዱ ጉራ በበኩላቸው፤ ሚኒስቴሩ ያደረገው ድጋፍ በመተጋገዝ ማህበራዊ ኀላፊነትን ከመወጣት ባለፈ አቅመ ደካሞችን መታደግ እንደሚቻል ጥሩ ማሳያ ነው ብለዋል።   ዛሬ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ለተደረገው ድጋፍ በከተማ አስተዳደሩ ሥም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የተሻለ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለመግባት ዝግጅት እያደረግን ነው- የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
Apr 23, 2026 67
ሰቆጣ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና የተሻለ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለመግባት ዝግጅት እያደረጉ እንደሚገኙ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ገለፁ። በሰቆጣ ከተማ የዋግ ስዩም አድማሱ ወሰን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ለምለም መኮንን ለኢዜአ እንደገለጸችው፤ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና የተሻለ ውጤት ለማምጣት ዝግጅት እያደረገች ትገኛለች።   ትምህርት ቤታቸው ከመደበኛው የትምህርት ክፍለ ጊዜ በተጨማሪ በትርፍ ጊዜያቸው የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት፣ ቤተመጻህፍትን ክፍት በማድረግና መጻህፍትን በማሟላት እገዛ እያደረገ መሆኑን ተናግራለች። በተጨማሪም ከክፍል ጓደኞቿ ጋር እርስ በእርስ በመረዳዳትና ያለፉትን ዓመታት የፈተና ጥያቄዎች በቡድን በመስራት የተሻለ ውጤት በማምጣት ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን አስረድታለች። ተማሪ ሳህለ ጊዮርጊስ ደባሹ በበኩሉ ለፈተናው ከተማሪዎች ጋር በመሆን እየተጋገዙ በቂ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ገልጿል።   መምህራንም በመደበኛው የትምህርት ጊዜ ለፈተናው በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ በሚያስችል መልኩ እውቀት እያስጨበጧቸው መሆኑን ተናግሯል። ትምህርት ቤቱ የዲጂታል መማሪያ ክፍል በማዘጋጀትም በኦን ላይን የሚሰጠውን ፈተና ቀድመው እንዲለማመዱ እያደረገ ነው ብሏል። በትምህርት ቤቱ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት ሰፊው ሃብቱ እንደገለጹት፤ ተፈታኝ ተማሪዎች ጊዜያቸውን በአግባቡ ተጠቅመው ለፈተናው በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ እገዛ እየተደረገ ነው።   ያለፉ የፈተና ጥያቄዎችን በማሰራት፣ በስነ ልቦና ዝግጁ እንዲሆኑ በማድረግና በፈተና ወቅት መረጋጋት አስፈላጊ መሆኑን በማስገንዘብ ዝግጅታቸውን ወደ ውጤት እንዲቀይሩት እያስረዳን እንገኛለን ብለዋል። የዋግ ብሔረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ምክትል ሃላፊ ወይዘሮ ፍትሃለሽ ምረቴ ፤ በአስተዳደሩ 3 ሺህ 506 ተማሪዎች የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደሚወስዱ ተናግረዋል።   ተፈታኝ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ የመርጃ መፅሀፍትን በማሟላት፣ ቤተ መጻህፍቱን እንዲጠቀሙ በማድረግና የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የማረሚያ ተቋማት የስብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል ሆነው እንዲያገለግሉ እየተሰራ ነው
Apr 23, 2026 68
ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረሚያ ተቋማት የስብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል ሆነው እንዲያገለግሉ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነሮች የጋራ ጉባኤ “የማረሚያ ተቋማት ለሀገር ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ መካሄድ ጀምሯል።   በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በክልሉ የማረሚያ ተቋማት የስብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል ሆነው እንዲያገለግሉ እየተሰራ ነው፡፡ በክልሉ ማረሚያ ቤቶች የሚገኙ ታራሚዎችን በስነ ምግባርና በክህሎት ለማነጽ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣ እነዚህ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። ዛሬ የተጀመረው የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ጉባኤ በክልሉ የተጀመረውን የሪፎርምና የተቋም ግንባታ ሥራን ለማጠናከር ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ብለዋል፡፡ ለሦስት ቀናት እየተካሄደ ባለው ጉባኤ በማረሚያ ቤቶች እየተከናወኑ ባሉ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ላይ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።   በተጨማሪም ከታራሚዎች የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ መሰረታዊ ፍላጎት አቅርቦት፣ ከማረሚያ ቤት የሪፎርም ሥራዎች እንዲሁም ከማረም ማነጽ ተሀድሶ ልማት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ጉባኤው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚመክር ታውቋል። በመድረኩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ፣ የፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ ከፍትህ ሚኒስቴር፣ ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን እንዲሁም ከክልል ማረሚያ ቤቶችና ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የመጡ የሥራ ኃላፊዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ኢኮኖሚ
በምስራቅ ጎጃም ዞን በፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ሆነዋል
Apr 23, 2026 18
ደብረ ማርቆስ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ፍራፍሬዎች ልማት ሥራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጨማሪ ገቢ በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገለጹ። በዞኑ ከ20 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በቆላና ደጋ የፍራፍሬ ተክሎች እየለማ መሆኑም ተመላክቷል። በምስራቅ ጎጃም ዞን የስናን ወረዳ አርሶ አደር ጌታሁን መንግስቴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከሰብል ልማት ሥራቸው ጎን ለጎን ከስምንት ዓመት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የአፕል ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ እያደረጋቸው ነው። በአሁኑ ወቅት ከሩብ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ልማቱን እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   በየዓመቱ ከሚሰበስቡት የአፕል ምርት እስከ 30 ሺህ ብር ተጨማሪ ገቢ እያገኙ እንደሆነና ቆጥበው ተጨማሪ ሃብት ለማፍራት እንዳገዛቸው ተናግረዋል። ዘንድሮም የአፕል ምርት አያያዙ የተሻለ መሆኑን ገልጸው፣ በምርት ሽያጩ ካለፈው ዓመት የተሻለ ገቢ ለማግኘት ተግተው እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዞኑ የጎዛምን ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር የሻነህ ጓዴ በበኩላቸው እንዳሉት ከአቮካዶ፣ ማንጎ እና ሎሚ ምርት ሽያጭ በዓመት ከ50 ሺህ ብር በላይ ገቢ እያገኙ ይገኛሉ። ከሰብል ልማት ሥራቸው ጎን ለጎን እያካሄዱት ያለው የፍራፍሬ ልማት ገቢያቸውን ከማሳደጉ ባሻገር ልጆቻቸውን የተመጣጠነ ምግብ ለመመገብና ጤናማ ሆነው እንዲያድጉ እያገዛቸው መሆኑን አስረድተዋል።   በምስራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባለሙያ ተሾመ በላይ፣ በዞኑ ከ20 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የፍራፍሬ ልማት እየተከናወነና በልማቱም አርሶ አደሮች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ዘንድሮ በዞኑ ከለማው አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ብርቱካን፣ ሎሚ፣ ፓፓያ፣ አፕልና ሌሎች የቆላና የደጋ ፍራፍሬዎች እስካሁን ከ80ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቦ ለገበያ መቅረቡን ጠቁመው፣ በቀሪ ወራትም የበለጠ ምርት ይቀርባል ብለዋል። ከፍራፍሬ ልማት የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ በመጪው የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የሚተከሉ ከ818 ሺህ በላይ የፍራፍሬ ችግኞች መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት በዞኑ ከፍራፍሬ ልማት ከ278ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለገበያ መቅረቡን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ
Apr 23, 2026 80
‎ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከነበረው ግትር ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አስተሳሰብ ተላቃ፣ ትኩረቱን በተግባራዊ አፈጻጸም ላይ ያደረገ አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ እይታ የተቃኘ የፖሊሲ ማዕቀፍ መከተል ከጀመረች ሰነባብታለች። ‎ይኅው አዲስ አቅጣጫ፤ ሀገሪቱ ለወቅታዊ የዓለምና የሀገር ውስጥ ነባራዊ ሁኔታዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራዊ መፍትሄዎችን እንድትቀይስ አስችሏታል። በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የሪፎርም ጉዞ፣ መንግሥትንና የግሉን ዘርፍ እንደ ወሳኝ አጋር በማየት፣ በውጤትና በውጤታማነት ላይ የተገነባ አዲስ የመንግሥት የሥራ ባህልን ተቋማዊ አድርጓል። ‎‎በዚህ ገቢር ነበብ እይታ አማካኝነት፣ በሚከተሉት ስምንት ቁልፍ ምሰሶዎች ወሳኝ ስኬቶች ተመዝግበዋል፦ ‎• በኢኮኖሚ ዕይታ ረገድ፦ የመንግሥትን ሚና ዳግም በመተርጎም፣ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና ዘርፈ-ብዙ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎች አማካኝነት የገበያ ውድድር እንዲሰፍንና የኢኮኖሚ አቅም እንዲጎለብት ተደርጓል። ‎• በአማራጭ ፋይናንስ ዘርፍ፦ የካፒታል ገበያ ልማትን በማብሰር፣ የመንግሥትና የግል አጋርነትን በማጠናከር እና ዘመናዊ የገንዘብ ገበያ በመፍጠር የሀገሪቱን የፋይናንስ አማራጮች ማሳደግ ተችሏል። ‎• በኢኮኖሚ አመራር በኩል፦ በመደበኛ ክትትልና ግምገማ፣ በማክሮ ኮሚቴና በዘርፍ ካውንስሎች የተቀናጀ አሰራር አማካኝነት የገንዘብ ፖሊሲና የፕሮጀክቶች አስተዳደር ይበልጥ ውጤታማና ቀልጣፋ እንዲሆን ተደርጓል። ‎• የግል ዘርፍ ሚናን በማሳደግ፦ የግሉ ዘርፍ ከማህበራዊ ኃላፊነት ባለፈ የኢኮኖሚው መሪና ዋና ሞተር እንዲሆን በማድረግ እንደ ትልቅ የልማት አጋር እንዲሳተፍ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል። ‎• በልማት አጋርነትና ንግድ ትስስር ፦ የብድር ሽግሽግና አዲስ ፋይናንስን በማረጋገጥ፣ ለዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት የሚደረገውን ሂደት በማፋጠንና የAfCFTA ትግበራን ውጤታማ በማድረግ የሀገሪቱ ዓለም አቀፋዊ የንግድ ተወዳዳሪነት ከፍ ብሏል። ‎• በማህበራዊ ደህንነት ረገድ፦ አካታችነትን፣ ተደራሽነትንና ጥራትን መሠረት ያደረገ የሰው ተኮር ድጋፍ ሥርዓት በመዘርጋት፣ የማህበራዊ ጥበቃ አገልግሎቶች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ማድረግ ተችሏል። ‎• በፍትሃዊ የመሰረተ ልማት ስርዓት ፦ የአካባቢ ጸጋን መሠረት ያደረገ፣ በግልጽ የሕግ ማዕቀፍ የሚመራና ያለፉ የፍትሃዊነት ክፍተቶችን የሚሞላ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥርዓት ተግባራዊ ሆኗል። ‎• በስርዓት ግንባታ በኩል፦ ብሔራዊ አካታች ምክክርን በማካሄድ፣ በፍትህና በሲቪል ሰርቪስ ዘርፎች ሪፎርም በማድረግ እንዲሁም የዲሞክራሲ ተቋማትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ውጤቶች ተመዝግበዋል። #PMOEthiopia
ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 35 ባለሀብቶችን ወደ ስራ አስገብቷል
Apr 23, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ፓርኮች ኮርፖሬሽን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 35 ባለሀብቶችን ተቀብሎ ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ገለጸ። ኮርፖሬሽኑ በተለይ የገቢ ምርቶችን በሚተኩ የልማት ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራቱም ውጤታማ ጅምር መኖሩን አረጋግጧል። በኮርፖሬሽኑ የልማት ዘርፍ ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ቱፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኮርፖሬሽኑ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የማልማት ፣ የማስተዳደርና ገቢ የማመንጨት ተልዕኮውን በስኬት እየተወጣ ይገኛል። በበጀት ዓመቱም ባለሀብቶች በቡልቡላ የተቀናጀ ኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ በመካከለኛ ኢንዱስትሪ ማዕከላት፣ ጥቃቅን ኢንዱስትሪ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ገቢን ለማመንጨትና ተኪ ምርቶችን ለማምረት ወደ ስራ መግባታቸውንም ነው የገለጹት።   ባለሀብቶቹ በዋናነት በምግብ ዘይት፣ በጥራጥሬና ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በተለያዩ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ላይ መሰማራታቸውን ተናግረዋል። ባለሀብቶቹ ስራ የጀመሩት መሰረተ ልማት በተሟላላቸው ስፍራዎች መሆኑን የገለጹት አቶ ሰለሞን፣ በዋናነትም የቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና በስሩ የሚገኙ 6 መካከለኛ ኢንዱስትሪ ማዕከላት መሆናቸውን ጠቁመዋል። በበጀት ዓመቱም 35 ባለሀብቶችን ወደ ማምረት ስራ ማስገባት በመቻሉ በአጠቃላይ የአልሚ ባለሀብቶች ቁጥር 81 ደርሷል ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት በኮርፖሬሽኑ ስር በሚገኙ ፓርኮች ተመርቶ ለገበያ የቀረበ ሲሆን፣ ከዚህም 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል።   ወደ ስራ በገቡት አምራች ኢንዱስትሪዎች 3 ሺህ 225 ዜጎች የስራ ዕድል ማግኘታቸውንም አስታውቀዋል። በነቀምቴ የተቀናጀ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከለማው 60 ሄክታር መሬት ውስጥ 10 ሄክታሩ ለባለሀብቶች የተላለፈ ሲሆን ከተገነቡት ሶስት ሼዶች መካከል ሁለቱ ለባለሀብቶች እንዲተላለፉ መደረጉንም ገልፀዋል። ኮርፖሬሽኑ በቀጣይም የለሙ መሬቶችን በማቅረብና አምራቾች ምርቶቻቸውን በስፋት ለገበያ እንዲያቀርቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ምክትል ስራ አስፈጻሚው አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል
Apr 23, 2026 59
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ይካሄዳል፡፡ የጎዳና ላይ ሩጫውን በተመለከተ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ታምርት የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ አስተባባሪ አብዱልፈታህ የሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ታምርት የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ይካሄዳል። የሩጫ ውድድሩ ገቢ ምርትን በመተካት የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የስፖርት አልባሳትን ማስተዋወቅ እና የማምረት አቅማቸውን ማሳየትን አላማ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ዜጎች የሀገር ውስጥ ምርትን የመጠቀም ባህል እንዲያሳድጉ ግንዛቤ የሚፈጠርበት መሆኑንም አመላክተዋል። ውድድሩ አዲስ አበባ ከተማ ያላትን የቱሪዝም ሀብት ለማስተዋወቅ ተጨማሪ እድል እንደሚፈጥርም እንዲሁ። በውድድሩ ከ15 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች እንደሚገኙ እና ከእነዚህ ውስጥ 500 የሚሆኑት አትሌቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህ ውድድር በሴቶችና በወንዶች 1ኛ ለሚወጡ 550 ሺህ ብር፣ 2ኛ ደረጃን ለሚይዙ 300 ሺህ ብር እንዲሁም በ3ኛነት ለሚያጠናቅቁ ደግሞ 200 ሺህ ብር እንደሚበረከት ተናግረዋል። በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተሳትፎና ውድድር ዳይሬክቶሬት ተወካይ ጊዜ አድነው በበኩላቸው፤ የጎዳና ላይ ሩጫው ለአትሌቶች አዲስ የውድድር እድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ዘርፍ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል ቁርጠኝነቷን ዳግም ታረጋግጣለች 
Apr 23, 2026 86
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ዘርፍ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል ቁርጠኝነቷን ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ መራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነትም እንዲሁ ዳግም ታረጋግጣለች ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን አዲስ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ጠዋት የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በውይይታችንም በተለያዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የመከርን ሲሆን፤ በተለይም በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ነው ያሉት። በዚህም ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ መራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉ ገልጸዋል። የፈጠራ ሥራዎች ለአፍሪካ ዕድገት ምንጊዜም ወሳኝ መሰረት መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ጠቁመዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ መራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ቁርጠኛ መሆኗንም ገልጸዋል። ይህንን ርዕይ ወደ ተጨባጭና አካታች ውጤት ለመለወጥ ከአፍሪካ ሲዲሲ (Africa CDC) እና በመላው አህጉሪቱ ከሚገኙ አጋሮች ጋር በቅርበት ለመሥራት ዝግጁ ነኝ ሲሉም አረጋግጠዋል።
ለህብረተሰቡ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅተናል
Apr 23, 2026 62
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ ለህብረተሰቡ የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መንገድ ለመስጠት ተዘጋጅተናል ሲሉ የመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ሰራተኞች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአይነቱ ልዩና የመጀመሪያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት አስጀምረዋል። በአገልግሎቱ የስምንት ተቋማትን አገልግሎቶች በአንድ ላይ በማቀናጀት በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን፤ ይህም ለህዝብ የሚሰጡ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን ይበልጥ ተደራሽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።   በዚህ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት የተጀመሩ አገልግሎቶችም፣ የገቢ (አዲስ ቲን ማውጣት)፣ የንግድ (ንግድ ፈቃድ ማውጣት፣ ማደስ)፣ የጤና (ለመንጃ ፈቃድ አካላዊ የጤና ምርመራ)፣ የሲቪል ምዝገባ (የመታወቂያ ዕድሳት እና ልደት)፣ የአሸከረካሪ ተሽከርካሪ (የመንጃ ፈቃድ እና የቦሎ ዕድሳት)፣ የኢትዮ ፖስታ (የመንገድ ፈንድ ክፍያ)፣ የብሔራዊ መታወቂያ (አዲስ ምዝገባና የመረጃ እርማት) እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት (ቅድመ ክፍያ) ናቸው። በመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት እንዲሰጡ የተመደቡ የልዩ ልዩ ተቋማት ሰራተኞች፣ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በዘመናዊና ቀልጣፋ መንገድ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። በሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የአዲስ መሶብ አገልግሎት አስተባባሪ ዳኜ መኮንን ኤጀንሲው በተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ላይ ለህብረተሰቡ ከሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ጋር የተገናኙ አስር ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን ለመስጠት ወደ ስራ ገብተናል ብለዋል።   ለአገልግሎት ፈላጊ ደንበኞች ከሚሰጧቸው አገልግሎቶች መካከል የዲጂታል መታወቂያ እድሳት፣ የልደት ካርድ ማውጣት፣ የጉዲፈቻና ያላገባ ሰርተፊኬት መስጠት ተጠቃሽ መሆናቸውን አብራርተዋል። የመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ውስጥ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የደንበኞች አገልግሎት ባለሙያ አስናቀ ወርቁ በበኩላቸው፣ ባለስልጣኑ በማዕከሉ የመንጃ ፈቃድ እድሳትን፣ የዓመታዊ የብቃት ማረጋገጫ ቦሎና የተበላሸ ቦሎ ግልባጭ እንዲሁም የጠፋ ቦሎ ምትክ የመስጠት አገልግሎቶችን ለደንበኞች እንደሚያቀርብ ገልጸዋል።   በመሶብ ተንቀሳቃሽ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የጤና ምርመራ ዘርፍ የሚያገለግሉት አቶ ጉቱ ከበደ በበኩላቸው፤ በተለይም ለመንጃ ፈቃድ ዕድሳት የሚመጡ ደንበኞችን ጨምሮ ለተለያዩ አገልግሎቶች አስፈላጊ የጤና ምርመራዎችን በማድረግ ላይ እንገኛለን ብለዋል።   በገቢዎች ቢሮ የደንበኞች አገልግሎት ባለሙያ ጫልቱ ታደሰ፣ ቢሮው ከሚሰጣቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች መካከል በዋናነት የሚጠቀሰውን የንግድ መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) የመስጠት ተግባር በተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አማካኝነት ለነዋሪዎች እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ ፖስታ ባለሙያ ሙላቷ አበዙ ድርጅታቸው በመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ውስጥ የመንገድ ፈንድ አገልግሎት እና የፋይዳ መታወቂያ ህትመት የሚፈልጉ ደንበኞችን ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ተናግራለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው ተሾሙ
Apr 23, 2026 151
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሹመዋል። ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች የምትገኘውን የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በተላከው የሹመት ደብዳቤ ላይ "የተከበሩ የእርስዎ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ አድርጓል" የሚል ሀሳብ መስፈሩን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። "ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል" የሚል መልዕክትም በተላከው የሹመት ደብዳቤ ላይ ሰፍሯል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር፣ ኢትዮጵያ በዲጂታላይዜሽን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች ያስመዘገበችው እድገት ከፍተኛ አፈጻጸም ማሳየቱን ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኢ-መንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል፣ በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩትን ማቋቋም እንዲሁም ሀገራዊ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ መንደፍ ለለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውንም አክሎ ገልጿል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የታቀደው ዕቅድ፤ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
በሐረሪ ክልል ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ወስደዋል
Apr 23, 2026 108
ሐረር፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የክልሉ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ገለጸ። የሐረሪ ክልል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ሃላፊና የክልሉ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አስተባባሪ ሳዳም መሐመድ እንደገለጹት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በክልሉ የከተማና ገጠር ወረዳዎች ተደራሽ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም ባለፉት 9 ወራት ብቻ ከ180 ሺህ በላይ ዜጎች መታወቂያውን መውሰዳቸውንና በአጠቃላይ በእስካሁኑ ሂደት ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች መታወቂያውን መውሰዳቸውን ጠቅሰዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መሳካት ጉልህ አበርክቶ አለው ሲሉም ገልጸዋል። በተለይም የዲጂታል ማንነት መለያ ተቋማት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ በማስቻል ግልፅነትና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። መታወቂያው በአገልግሎት ሰጪና ተቀባዩ መካከል ይበልጥ መተማመን እንዲኖር የሚያስችል፣ የተቋማትን ሥራ የሚያቀናጅ፣ በግለሰቦች ደረጃም የራስን መብት የሚያስጠብቅ መሆኑንም አክለዋል። በተለያዩ ምክንያቶች ምዝገባ ያላካሄዱ የማህበረሰብ ክፍሎችም በአቅራቢያቸው በሚገኙ የምዝገባ ማዕከላት አገልግሎቱን እንዲጠቀሙ ሃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።
ስፖርት
ማንችስተር ሲቲ የሊጉን መሪነት ከአርሰናል ተረከበ
Apr 23, 2026 205
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018 (ኢዜአ):- በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ማንችስተር ሲቲ በርንሌይን 1 ለ 0 አሸንፏል።   በተርፍ ሙር ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አርሊንግ ሃላንድ በአምስተኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ግቧን አስቆጥሯል። በጨዋታው ማንችስተር ሲቲ ከፍተኛ ብልጫ ቢወስድም ያገኛቸውን ግልጽ የግብ እድሎች መጠቀም አልቻለም። ባለሜዳው በርንሌይ በጥልቀት የመከላከል እና የመልሶ ማጥቃት እንቅስቃሴን አድርጓል። በሊጉ 21ኛ ድሉን ያስመዘገበው ማንችስተር ሲቲ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ70 ነጥብ የሊጉን መሪነት ከአርሰናል ተረክቧል። ሁለቱም ክለቦች በተመሳሳይ 70 ነጥብ እና 37 የግብ ክፍያ ቢኖራቸውም ማንችስተር ሲቲ ባስቆጠረው የጎል ብዛት (66) የሊጉ መሪ ሆኗል። አርሰናል ወደ ሁለተኛ ደረጃ ዝቅ ብሏል። የሲቲ ማሸነፍ የሊጉን የዋንጫ ፉክክር ይበልጥ አጓጊ አድርጎታል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 22ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው በርንሌይ በ20 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በርንሌይ አራት ጨዋታዎች እየቀሩት ከፕሪሚየር ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል። ዎልቭስ ከሊጉ አስቀድሞ መውረዱ የተረጋገጠ ክለብ ነው።   በሌላኛው መርሐ ግብር ቦርንማውዝ እና ሊድስ ዩናይትድ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። በቫይታሊቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጁኒየር ክሩፒ እና ራያን ግቦቹን ለቦርንማውዝ አስቆጥረዋል። ሲን ሎንግስታፍ እና የቦርንማውዙ ጀምስ ሂል በራሱ ላይ ለሊድስ ዩናይትድ ብቸኛውን ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ቦርንማውዝ በ49 ነጥብ ደረጃውን ከዘጠነኛ ወደ ሰባተኛ ከፍ አድርጓል። ባለፉት 14 የሊጉ ጨዋታዎች ያልተሸነፈው ቦርንማውዝ በጠንካራ ግስጋሴ ላይ ይገኛል። ሊድስ ዩናይትድ በ40 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡድኑ ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ አንድ ነጥብ አግኝቷል።
ቼልሲ ሊያም ሮሲኒየርን አሰናበተ
Apr 22, 2026 514
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፦ የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ዋና አሰልጣኙን ሊያም ሮሲኒየርን ከኃላፊነት ማሰናበቱን በይፋ አስታውቋል። አሰልጣኙ በስታምፎርድ ብሪጅ በነበራቸው ቆይታ ክለቡን መምራት የቻሉት ለአራት ወራት ብቻ ሲሆን፣ ይህ ውሳኔ የተላለፈው ቡድኑ እያሳየ ባለው እጅግ ደካማ ውጤት ምክንያት መሆኑን ቢቢሲ ክለቡን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል። በሮሲኒየር መሪነት ቼልሲ ካለፉት ዘጠኝ የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው በአንዱ ብቻ ሲሆን፣ በተለይም ባለፉት አምስት ጨዋታዎች ቡድኑ ምንም አይነት ግብ ሳያስቆጥር መሸነፉ ለአመራሮቹ ትዕግስት ማጣት ዋነኛ ምክንያት መሆኑ ተገልጿል። ቼልሲ ትናንት በሊጉ በብራይተን 3 ለ 0 መሸነፉ ይታወቃል። ሮሲኒየር የስድስት ዓመት ተኩል ረጅም ኮንትራት ፈርመው ወደ ክለቡ ቢመጡም፣ ቼልሲን በደረጃ ሰንጠረዡ ወደ ሰባተኛ ደረጃ ዝቅ ማድረጋቸው እና የቻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ እድላቸውን አደጋ ላይ መጣላቸው ለስንብቱ ምክንያት ሆኗል። ክለቡ ለሮሲኒየር እና ለረዳቶቻቸው በቆይታቸው ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋናውን አቅርቧል። በመጪው እሁድ ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ለሚያደርገው የኤፍ ኤ ካፕ (FA Cup) የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ፣ ካሉም ማክፋርሌን ቡድኑን በጊዜያዊ አሰልጣኝነት እንደሚመሩ ክለቡ አስታውቋል። ቼልሲ በአሁኑ ወቅት ቋሚ አሰልጣኝ ለመቅጠር ጥረት እያደረገ ሲሆን፣ ይህም በባለቤቱ ቶድ ቦህሊ ዘመን አምስተኛው አሰልጣኝ እንደሚሆን ቢቢሲ ዘግቧል።
አትሌት ገመኔ ማሚቴ ምትኩ በተከለከለ አበረታች ቅመም ምክንያት የስድስት ዓመት እገዳ ተጣለባት 
Apr 22, 2026 358
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን አትሌት ገመኔ ማሚቴ ቱኩ የተከለከሉ አበረታች ቅመሞችን (Doping) ተጠቅማ በመገኘቷ የስድስት ዓመት የእገዳ ቅጣት እንደተጣለባት አስታወቀ። ባለስልጣኑ በሁለት የተለያዩ ውድድሮች ላይ ባካሄዳቸው ምርመራዎች፣ አትሌቷ ኤሪትሮፖይቲን (EPO) እና ዴክሳሜታሶን (Dexamethasone) የተባሉ የተከለከሉ ንጥረ ነገሮችን መጠቀምዋን ማረጋገጡን አመልክቷል። በዚህም መሠረት አትሌት ገመኔ ማሚቴ ቱኩ ጊዜያዊ እገዳ ከተጣለባት ጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓ.ም (November 11, 2025) ጀምሮ ለስድስት ዓመታት የሚጸና፣ በማንኛውም ስፖርታዊ ውድድር እንዳትሳተፍ እገዳ መጣሉን ገልጿል። በተጨማሪም አትሌቷ ከግንቦት 3 ቀን 2017 ዓ.ም (May 11, 2025) ጀምሮ በተካሄዱ የተለያዩ ውድድሮች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች በሙሉ እንዲሰረዙ ተወስኗል። ይህም ሜዳሊያዎችን፣ የማዕረግ ስሞችን፣ ደረጃዎችን እና የሽልማት ገንዘቦችን መመለስን እንደሚጨምር ነው ባለስልጣኑ ያስታወቀው። በቀጣይም በሀገሪቱ በየደረጃው የሚደረገው የምርመራና ቁጥጥር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተመልክቷል። የኢትዮጵያ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን የስፖርት አበረታች ቅመሞችን በመጠቀምም ሆነ በተለያየ መልኩ የፀረ-አበረታች ቅመሞች የህግ ጥሰት በሚፈጽሙ አትሌቶችና ከጀርባ ሆነው በሚያበረታቱ ሌሎች ግለሰቦች ላይ የሚወሰደው የእርምት እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
አካባቢ ጥበቃ
በምሥራቅ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ ነው
Apr 23, 2026 72
ነቀምቴ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦በምሥራቅ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። በጽሕፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ በለጠ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ ነው።   በዘንድሮው መርሐ ግብር ለሁሉም የችግኝ ዓይነቶች ትኩረት ቢሰጥም፣ ይበልጥ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ዝርያዎች ላይ ትኩረት ተደርጓል ነው ያሉት። እየፈሉ ከሚገኙት ችግኞች መካከል አትክልትና ፍራፍሬ፣ የደንና ጥምር ደን ዝርያዎች፣ ቀርከሃ፣ የእንስሳት መኖ የሚገኙበት መሆኑን ነው የተናገሩት። የእጽዋት ስብጥሩ ከአካባቢው አየር ንብረት ጋር የሚስማማና በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤት የሚሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ካለፉት ዓመታት ተሞክሮ በመነሳት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የጉድጓድ ዝግጅት መጀመሩን የጠቆሙት አቶ ደሳለኝ፤ የአየር ንብረት ጥናት፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ እንዲሁም የሕብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያሳድጉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። ለዘንድሮው ተከላ የሚውል 107 ሺህ ሄክታር መሬት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በዞኑ በሚገኙ 2 ሺህ 194 የመንግሥትና የግል የችግኝ ጣቢያዎችም የችግኝ እንክብካቤ ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው ችግኝ መትከል ከመደበኛ መርሐ ግብር ባለፈ የሥራ ባሕላቸው እየሆነ መምጣቱን ይናገራሉ።   አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ወይዘሮ አዲስዓለም በለጠ ባለፉት ዓመታት በተተከሉ ችግኞች በአካባቢው የተፈጥሮ ሀብት ለውጥ መታየቱን ገልጸዋል። አቶ ተሰማ መኮንንም በተመሳሳይ ቀደም ሲል ለደን የነበረው ዝቅተኛ አመለካከት ተቀይሮ፣ ዛሬ ሕብረተሰቡ የተራቆቱ ቦታዎችን መልሶ በማልማትና በመንከባከብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   ለዘንድሮው ተከላም አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው
Apr 22, 2026 113
ሐዋሳ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (AGRA) የቦርድ ሊቀመንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ።   ሊቀመንበሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ ከሀገር ባለፈ አህጉራዊ የልማት ትብብርና ትስስርን መሰረት ባደረገ መልኩ በስኬት መቀጠሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂዋ ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እና የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይም ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች አስደናቂ መሆናቸውን አውስተው፤ እንደ ሀገር ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው የተፈጥሮ ሃብትን ከመጠበቅና የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትና መሰረት መሆናቸው በተግባር ታይቷል ብለዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ነው ያመላከቱት።   ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ላይ ትኩረት ተደርጎ መሠራቱም ለግብርና ልማትና ምርታማነት መሰረት እየሆነ መጥቷል ነው ያሉት። የዘርፉ ልማት ቀጣይነትን የሚጠይቅ በመሆኑ ችግኞችን መትከል እንዳለ ሆኖ፤ የተተከሉትን የመጠበቅና የመንከባከብ ልምድ እየዳበረ መሄድ እንዳለበትም ጠቁመዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ ሥራዎች አርሶ አደሩን ተጠቃሚ አድርገዋል
Apr 21, 2026 308
ወላይታ ሶዶ፤ሚያዚያ 13/2018(ኢዜአ)፦በወላይታ ሶዶ ከተማ በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። በከተማ አስተዳደሩ "አረንጓዴ አሻራ ለተምሳሌት ሀገር ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል የዘንድሮ የበልግ ወቅት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በመርካቶ ክፍለ ከተማ ቦሳ ዝጋ ቀበሌ ተካሂዷል። የከተማው ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማርያም በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት ባላፉት የለውጡ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት አረጋግጠዋል። በመርሀ ግብሩ የተተከሉ ችግኞች የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ በተጨማሪ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና ሚዛኑን ለመጠበቅ እያገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም የችግኝ ተከላ ሥራውን ለማስቀጠል የቡና፣ የእንሰት የአቮካዶና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል ሙሉ ዝግጅት በማድረግ ወደ ሥራ መገባቱንም ተናግረዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ንጋቱ ቡሹራ በበኩላቸው ባለፉት ዓመታት በተሰሩ የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል። ለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ለተከላ ከተዘጋጁ ችግኞች ውስጥ 150 ሺህ የሚሆኑት የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ችግኞች መሆናቸውንም አመልክተዋል። ከዚህ በተጨማሪ ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ የእንሰት፣ የአቮካዶ እና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ነው የገለጹት። የሚተከሉ ችግኞች ውጤታማ እንዲሆኑም የተጠናከረ የባለሙያዎች ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል። በመርሀ ግብሩ ላይ ከተሳተፉ አርሶ አደሮች አቶ ደበላ ዳና እና አቶ ኤልያስ ጁና በውሃ ገብ መሬቶችና እና በእርሻ ማሳቸው ላይ ባህር ዛፎችን እና ያረጁ ቡናዎችን በመተካት ልማቱን ማከናወናቸውን ጠቁመዋል። በችግኝ ተከላው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ፍራፍሬዎችን በመትከል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው በዞኑ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን አንስተዋል። በዘንድሮ የአረንጎዴ አሻራ መርሃግብርም የቡና ችግኝ በስፋት ለመትከል ዝግጅት መደረጉን ነው የገለጹት። አርሶ አደሮችም በመርሀግብሩ ቡናና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞችን ተክለው በመንከባከብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያሳድጉ አሳስበዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የዞንና የከተማ የመንግስት ሥራ ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎች እንዲሁም አርሶ አደሮች ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የወሰደቻቸው ተጨባጭ እርምጃዎች ውጤት እያስገኙ ነው
Apr 21, 2026 162
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የወሰደቻቸው ተጨባጭ እርምጃዎች ውጤት እያስገኙ መሆኑን የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የሚቲዎሮሎጂ ሶሳይቲ ጋር በመተባበር ለመጀመሪያ ጊዜ ያዘጋጀውን ሳይንሳዊ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው፡፡   የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና በዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዚዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ለዘርፉ ተስማሚ የሆኑ የኃይል አማራጮችንና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን በተግባር እያከናወነች ትገኛለች፡፡ ለዚህም እንደ አብነት ከሚጠቀሱት መካከልም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታዳሽ ኃይል ልማት ተምሳሌትና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ግንባታ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተተገበረ ያለው የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና የደን ልማት ስራዎች ተጨባጭ መፍትሄዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ድንበር ተሻጋሪ በመሆኑ ተጽዕኖውን ለመቋቋም የጋራ ጥረትና ትብብር መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከኮንፈረንሱ ለአፍሪካ ውጤታማ የሆኑ ሳይንሳዊ መፍትሄዎች እንደሚገኙም ገልጸዋል፡፡   የአፍሪካ የሚቲዎሮሎጂ ሶሳይቲ የቦርድ ሰብሳቢ ቡሩሃኒ ናይንዚ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ሶሳይቲው የተቋቋመው ሀገር አቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ማህበራትን ለማጠናከርና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎችን ለማስተሳሰር መሆኑን ገልጸዋል። ሳይንሳዊ ኮንፈረንሱ በአካባቢ ጥበቃ፣ በአየር ትንበያና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚሰሩ ተቋማትና ባለድርሻ አካላትን እንደሚያገናኝም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም የልምድና የዕውቀት ልውውጥ በማድረግ የባለሙያዎችን አቅም እንደሚገነባ ጠቅሰው በአፍሪካ የሚቲዎሮሎጂ ሳይንስ እድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል፡፡ ይህ ኮንፈረንስ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ያላትን ተሞክሮ ለማካፈል እንደሚረዳም ተጠቁሟል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 472
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 382
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 671
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት።   ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።   የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው 
Mar 22, 2026 365
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 19, 2026 320
የምግብ ሉዓላዊነት - ከተረጂነት መላቀቂያው መንገድ በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ ከተረጂነትና ጠባቂነት መፋቻ መንገዶች መካከል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አንዱ ብልኀት አድርጋ እየታተረች ነው። ይህን ተከትሎም የዜጎችን የምግብ ፍላጎት በራስ የምርት ዐቅም የመሸፈን ሥራ በመከወን ከጠባቂነት ለመላቀቅ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ስኬታማ ናቸው። ለዚህም ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ከልመና ወጥታ ወደ ውጭ ገበያ መላክ መጀመሯ አሥረጅ ነው። በመሆኑም ከውጭ የኢኮኖሚ ጥገኝነት በመላቀቅ የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት ለማስከበር በስንዴ ልማት የተመዘገበውን ስኬት በሌሎች የግብርና ዘርፎች ለመድገም ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም መሠረት በሩዝ፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ሻይ ቅጠል እና ሌሎች የተለያዩ ሰብሎች ላይ እየተከናወነ ያለው ሥራ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው። የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የግብርና ድርጅት (ፋኦ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምግብ ዋስትናና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ የአመራር ቁርጠኝነት የአግሪኮላ ሜዳሊያ በ2016 ዓ.ም ማበርከቱ ለምግብ ሉዓላዊነት ጥረት የተሰጠ ዕውቅና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ረሃብን ከማስቀረት ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ብሔራዊ ብልጽግናን ዕውን ለማድረግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሃብቶች፣ተስማሚ የዓየር ንብረት፣ ለሥራ ትጉ የሆነ ወጣት እንዳላት እና እነዚህን ሃብቶች ታሳቢ በማድረግ የታሪክ ዐውራ የሆነችውን ሀገር ልማት ወደፊት ለማራመድ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ እንደከፈልን ሁሉ፤ ከምግብ ጥገኝነት ለመላቀቅ በትጋት መሥራት ይገባል ሲሉ ማስገንዘባቸው ይታወሳል። የምግብ ሉዓላዊነት፣የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት፣ የበጀት ሉዓላዊነት ታላቁን የሀገር ሉዓላዊነት በጽናት የሚያቆሙ መሆናቸውንም አብራርተዋል። እነዚህን የሉዓላዊነት ዘርፎች ለማስከበርም ብሔራዊ ዐርበኝነት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። ሀገራዊ ትልሙ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት የሚያሸጋግር መልካም ጅማሮ ነው።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 19, 2026 151
ክልሎች፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የንፋስ ሃይል በቀጥታ የምናመራው በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ ነው። በኢተያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው የመረቁትን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን እንመለከታለን። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 100 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል ልማት ወደ ፊት እየተራመደች መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ሥራ ነው። ኢትዮጵያ ዘንድሮ ከጉባ እስከ አሰላ፣ ገናሌ እና አይሻ በሃይል ልማት ዘርፍ ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ፕሮጀክቶች አስመርቃለች። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ደግሞ በዚህ ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀምሯል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩም በምርቃቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ከለውጡ በፊት የነበረው 4 ሺህ ሜጋ ዋት የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በመድረስ ከእጥፍ በላይ እድገት የተመዘገበበትን ትልቅ ስኬት አንስተዋል። የስንዴና ገብስ ሰብሎችን በከፍተኛ መጠን የሚያመርተው አርሲና አካባቢው አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ሃይል የሚመረትበት አካባቢ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እናስቀጥላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። ቢሾፍቱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማም በዚህ ሳምንት በቢሾፍቱ ሀርሰዴ አዳራሽ መካሄዱ ይታወቃል። በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ስኬታማ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይም የክልሉን ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ የከተማ እና የገጠር የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ነው ያስረዱት።   ከዚህ ባለፈ የክልሉን የልማት ሥራዎች ለማቀላጠፍ የሚያግዙ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የአገልግሎት አሰጣጥ አሰራሮች መተግበራቸውንም ተናግረዋል። የቢሾፍቱ መድረክ በድምሩ የግብርና፣ የገጠርና የከተሞች ልማት፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ክንውን በዝርዝር የታየበት ውጤታማ መድረክ እንደነበረም ተመላክቷል። የአሎማ ክላስተር ሌላ የሳምንቱ ዓበይት ጉዳይ ወደ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ይወስደናል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በይፋ አገልግሎት መስጠት የጀመረው በዚህ ሳምንት ነው። በመስኖ የለማ የስንዴ ክላስተር የተጎበኘበትና በተሁለደሬ ወረዳ በክላስተር ለሚከናወነው የተቀናጀ የፍራፍሬ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ የተጀመረበት እንዲሁም የክልሉ የ10 ዓመት የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገበትን ሁነት እናገኛለን።   በእነዚህ ሁነቶች ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የመደመር መንግሥት በሁሉም ዘርፎች ለሀገር እድገትና ማንሰራራት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም በግብርና፣ በመስኖ ልማት፣ በቱሪዝምና ሌሎች መስኮች በተግባር የተመለከትናቸው የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። የአሎማ ክላስተር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የሓይቅ ዳር አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የማቻል ጥረት በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን የሚያሳዩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሀገርን የማሻገር ሥራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የታሪክ መሰነጃ የሳምንቱ በረራችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ የሰው ልጅ መገኛ፣ የኤርታሌ ትኩሳት የሚገነፍልባትና የአዋሽ ወንዝ የተንጣለለባት አፋር ክልል ገብተናል። በአፋር ቆይታችን ትኩረታችንን ሰመራ በማድረግ በስፍራው ሊገነባ የታሰበውን የሉሲ ሙዚየም እንመለከታለን። ሙዚየሙን ለመገንባት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እና የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ የፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት አድርገዋል። ለሉሲ አፋር ቤቷ ነው፤ ሀዳር የተባለው ስፍራ ደግሞ መገኛዋ ነው። በመሆኑም በዚህ ከሰው ልጅ መገኛ ጋር የተቆራኘን ስፍራ ሙዚየም ገንብቶ፣ የቱሪስት መስህብ አልምቶና አካባቢውን በስፋት አስተዋውቆ የገቢ ምንጭ ማድረግ ሲቻል ለምን ተዘንግቶ ቆየ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ይሆናል። የጊዜ ጉዳይ ሆኖ አሁን አፋር ሰመራ ላይ በሉሲ የተሰየመ የሀገር ታሪክና ቅርስ ማጣቀሻ፤ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ማሳያ የሆነ ሙዚየም ለመገንባት ዝግጅት መደረጉ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል።   የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር)፤ የሚገነባው ሙዚየም የሀገር ታሪክና ቅርስ የሚሰነድበት፣ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ተጠብቀው የሚዘልቁበት፣ የሰው ልጅ አመጣጥና ዝግመተ ለውጥ የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ የሚካሄድበት ይሆናል ብለዋል። እሳቸው እንዳሉት የሙዚየሙ ግንባታ በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገለግሎት የሚበቃ ይሆናል። የአፋር ክልል በመስኖ ቢያለሙበት፣ የጥጥ እና የቴምር ልማት ቢካሄድበት ተዝቆ የማያልቅ እምቅ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በለውጡ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን እምቅ የቱሪዝም ሃብቱንም በማልማትና በመጠበቅ የሃገር ሃብት የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የሉሲ ሙዚየም ግንባታ ሁነኛ ማሳያ ነው። የሳምንቱ ቅኝታችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ በቀጥታ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝተናል። አሶሳ በሳምንቱ በሃይማኖት አባቶች ጸሎትና ዱአ ተባርካ ስለ ሰላምና አብሮነት የሚመከርባት ከተማ ሆና እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። የተለያዩ የኃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት 7ኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ "ሰላምን ይበልጥ ለማስፋት እና ለማስረጽ የሃይማኖቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ አባቶች ስለ ሰላም እና አብሮነት እንትጋ ለትውልድ ግንባታም መስራት ግድ ይለናል በማለት አፅንኦት በመስጠት መክረዋል።   የኢትዮጵያ ሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኃይማኖቶች ለሰላም እና ለህዝቦች አብሮነት ያላቸውን አስተምህሮ በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ እና ሀገራዊ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን አለባቸው ብለዋል። በኢትዮጵያ ሰላምን ለማጽናት እና የወንድማማችነት ድልድይን ለመገንባት እንስራ በማለትም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ስንጓዝ የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ-AGRA) ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የኤልቶ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ዩኒየን የሥራ እንቅስቃሴን መጎብኘታቸውን እናገኛለን። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጥምረቱ የቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ አርሶ አደሮች ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ጥሩ ተስፋ የተሰነቀበት መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። የግብርና ልማትን የማዘመን፣ ምርታማነትን የማሳደግና የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል።   የጥምረቱ ፕሬዚዳንት አሊስ ሩህዌዛ፤ በአፍሪካ የግብርና ስርዓት ሽግግርን ለማጠናከር በተለይም አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። በአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ሂደት ውስጥ ደግሞ የኢትዮጵያ ለውጥ አስደናቂ ስለመሆኑ አንስተዋል። ሌሎች በዚህ ሳምንት በሁሉም ክልሎች ባደረግነው ምልክታ በተለይም የምርጫ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኖ ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን እየወሰዱ ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎችም የምረጡኝ ቅስቃሳ ማድርጋቸውን ቀጥለዋል። የግብርና ልማት ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እና ሌሎችም የልማት ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ የቀጠሉበት ሳምንት ነበር ማለት ይቻላል።
የጤና ነገር …
Apr 17, 2026 350
በዮሐንስ ደርበው ማዲያት ታክሞ ይድናል? እነማንንስ ያጠቃል? የሥነ-ውበት ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ሱመያ ኑርሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለማዲያት መንስዔ፣ ምልክቶች እና ሕክምና ሙያዊ ሐሳባቸውን አጋርተዋል። እንደ ባለሙያ ቢደረግ ያሉትንም መክረዋል። • ማዲያት እነማንን ያጠቃል? ማዲያት ማንኛውንም ሰው እንደሚያጠቃ ያነሱት ዶ/ር ሱመያ፤ በብዛት ግን በሴቶች ላይ እንደሚከሰት ያስረዳሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ እርግዝና ላይ ያሉ እንዲሁም የወሊድ መከላከያ የሚወስዱ ሴቶች እና ሆርሞናል ቴራፒ ላይ ያሉ ሰዎች በስፋት ለማዲያት ተጋላጭ ናቸው። በተጨማሪም በብዛት ምግብ ማብሰል (ኪችን) ላይ የሚሠሩ ሰዎች ለማዲያት እንደሚጋለጡ ጠቁመዋል። ባብዛኛው ማዲያት የሚያጠቃው በዕድሜ ከ25 ወይም ከ30ዎቹ በላይ የሆኑትን መሆኑንም አንስተዋል። • መንስዔ እንደ ዶክተር ሱመያ ገለጻ፤ ለማዲያት ከሚያጋልጡ መንስዔዎች መካከል ዋነኛው የፀሐይ ጨረር ነው። በተጨማሪም ሆርሞናል ፋክተር (የወሊድ መከላከያ መጠቀም፣ እርግዝና ላይ መሆን፣ ሆርሞናል ቴራፒ መውሰድ) ለማዲያት አጋላጭ መንስዔ ሆነው ይጠቀሳሉ ይላሉ። ጭንቀት እንዲሁም ቆዳን የሚያስቆጡ ነገሮች ለማዲያት አጋላጭ መሆናቸውንም ነው ያብራሩት። • ምልክቶች ማዲያት ቀላ፣ ጠቆር ወይም ደብዘዝ ያለ ቀለም (መልክ) ይዞ ከትንሽ ጀምሮ የሚሰፋ መሆኑን ዶክተር ሱመያ አስገንዝበዋል። ለምሳሌ ይላሉ፤ ጉንጭ ላይ መውጣት ቢጀምር ወደ ሁለቱም ጉንጮች ከዚያም ወደ ግንባር እንዲሁም አገጭ እና አፍንጫ ሊደርስ እንደሚችል ገልጸዋል። በሂደትም የማቃጠል፣ የመቆጥቆጥ እና ማሳከክ ሁኔታ ሊኖረው እንደሚችል ነው ያነሱት። • ሕክምና መንስዔዎቹን ዐውቆ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ያስገነዘቡት ዶክተር ሱመያ፤ የፀሐይ ጨረር መከላከያዎችን መጠቀም፣ በሕክምና የሚሰጡ መድኃኒቶችን ሳያቋርጡ በትዕግስት መጨረስ (ቶሎ ለውጥ አላየሁበትም ብሎ አለማቋረጥ) እንደሚገባም መክረዋል። የማዲያት ሕክምና ስኬታማነቱ ለሁሉም ሰው በዕኩል ጊዜ እንደማይታይ በመግለጽ፤ እንደተከሰተበት ጊዜ ከሰው ሰው እንደሚለያይ በአጽኦት ተናግረዋል። ለምሳሌ አሉ፤ ዓመታት ያለፉት ማዲያት እና 2 ወራት የሆኑት ሕክምና እኩል ቢጀመርም በተመሳሳይ ጊዜ ላይድኑ እንደሚችሉ አመላክተዋል። ስለዚህ የሌላኛው ድኖ የኔ አልዳነም በሚል ሕክምናን ማቋረጥ ስህተት መሆኑንም ነው ያስረዱት። በሌላ በኩል ማዲያትን አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠው፤ ይህም የሚሆነው መንስዔዎቹን በማወቅ የማዲያት ተጋላጭ ባለመሆን ነው ብለዋል። ከተቻለ በየሥድስት ወሩ ወይም በየዓመቱ የቆዳ ጤና ምርመራ ማድረግ እና ያለበትን ደረጃ ማወቅም የሚከሰት ችግር ቢኖር እንኳ ሥር ሳይሰድድ በማከም ቶሎ እንዲድን ማድረግ ይቻላል ነው ያሉት።
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 13, 2026 225
በምግብ ራስን የመቻል ጉዞ አንዱ ምሰሶ - የስንዴ ልማት በሙሴ መለሰ ስንዴ በኢትዮጵያ በከፍትኛ ደረጀ ከሚመረቱና ለግብይት ከሚውሉ የሰብል ምርቶች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የስንዴ አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል በግንባር ቀደምነት ትጠቀሳለች። ከ2011/2012 የምርት ዘመን በፊት ኢትዮጵያ በመኸር የምታለማው ስንዴ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን ሔክታር ያልበለጠ ነበር። የበጋ መስኖ ስንዴ ሲጀመርም 3 ሺህ ሔክታር ብቻ እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በመኸር፣ በበጋ መስኖ እና በበልግ ወቅት 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ እያለማች እንደምትገኝ የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያስረዳል። ሚኒስቴሩ የ2018 ዓ.ም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ 4 ነጥብ 29 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ በማልማት ከበጋ መስኖ ስንዴ 175 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን መግለጹ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በአብዛኛው የስንዴ ምርት የሚመረተው በአነስተኛ አርሶ አደሮች ነው። ባለፉት ዓመታት ግን የሜካናይዝድ እርሻ የስንዴ ምርቱን በእጥፍ እንደጨመረው ይገለጻል። መንግሥት መስኖን በመጠቀም ስንዴን በዓመት አንድ ጊዜ ከማምረት ወደ ሦስት ጊዜ ማምረት የሚቻልበትን አሰራር በመፍጠር የሀገሪቱን ምርታማነት ለማሳደግ እየሠራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ107 ሚሊየን ኩንታል በላይ ነው። ይህንን ፍላጎቷን ለመሙላት ለዓመታት ከ700 ሚሊየን ዶላር እስከ 1 ቢሊየን ዶላር ለስንዴ ግዥ ወጪ ታደርግ ነበር። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ትሸፍን የነበረውም ከውጭ በምትገዛው ስንዴ ነበር። መንግሥት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በማስፋፋትና በየዓመቱ የሚመረትበትን ዙር በመጨመር ኢትዮጵያ የስንዴ ፍጆታዋን ሙሉ በሙሉ እንድትሸፍን በትኩረት ሲሠራ ቆይቷል። በዚሁ በ2014 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገር ስንዴ ማስገባት አቆመች። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያገኘችው ውጤት ከውጭ ማስገባትን ማስቆም ብቻ አልነበረም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ራስን ብቻ ሳይሆን ኤክስፖርት የማድረግ ዐቅም እንዳላት በመግለጽ፤ ስንዴ ወደ ውጪ መላክ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስቀመጡት ሀገራዊ ግብ መሰረት ኢትዮጵያ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ውጭ የመላክ ተግባርን በይፋ አስጀምራለች። የስንዴ ኤክስፖርቱ ኢትዮጵያ ገጽታዋን የሚለውጥ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ መግባቷን የሚያመላክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ገልጸው ነበር። ኢትዮጵያ በ2015 ዓ.ም የሀገር ውስጥ ፍጆታዋን ሸፍና 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ የማቅረብ ዐቅም እንዳላት ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚና የኤክስፖርት ኮሚቴ አረጋግጧል። ኮሚቴው የሀገራዊ የነፍስ ወከፍ ፍጆታና የሀገሪቱን አጠቃላይ የምርት ሚዛን በማጥናት ከፍጆታ የሚተርፍ 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ወደ ውጭ መላክ እንደሚቻልም ተገልጿል። 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ባሳለፍነው የካቲት ወር በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄዱ የሚታወስ ነው። በወቅቱም የአፍሪካ ሕብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ከጉባዔው ጎን ለጎን በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ ተምሳሌታዊ የሆነ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስንዴ ምርታማነቷን በማሳደግ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን ባለፈ ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሏን ሕብረቱ መመልከት መቻሉንም ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት በዓመት ውስጥ ለምግብ ምርቶች ከሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ ስንዴ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከውጭ የሚገባውን ምርት በሀገር ውስጥ ስንዴ መተካት እንደሚቻል በተግባር ያሳየችበት መንገድ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን ተሞክሮ ወስደው ወደ ተግባር እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ሥራ ላይ እያሳየች ያለውን ሥራ አስፍታ ከቀጠለች በምግብ ራሷን የመቻል ሕልሟን የማሳካት እድሏ ሰፊ መሆኑንም ማመላከታቸው ይታወሳል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ በአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ መንገድ
Apr 21, 2026 1426
(በዮሐንስ ደርበው) ታሪክ እንደሚነግረን፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ዕውቅና ያገኘው የኢንዱስትሪያዊ ንብረት ጥበቃን በሚመለከተው በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1883 በተፈረመው የፓሪስ ስምምነት እንዲሁም፤ በ1886 የተፈረመውን የሥነ-ጽሑፍና ሥነ-ጥበብ ሥራዎች ጥበቃን የተመለከተውን የበርን(ስዊዘርላንድ) ስምምነት ተከትሎ ነው። እነዚህ ስምምነቶችም በዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት የሚተዳደሩ መሆናቸው ይታወቃል። ኢትዮጵያ የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣንን፤ በ2022 ዓ.ም ፈጠራንና ኢኖቬሽንን በማበረታታት የፈጠራ ሐሳቦችን ወደ ዕሴት በመለወጥ ሂደት ለሀገራዊ ብልጽግና ቁልፍ ሚና የሚጫወት በአፍሪካ ተምሳሌት የአዕምሯዊ ንብረት ተቋም ለማድረግ እየታተረች ነው። ለዚህ ርዕይ መሳካትም፤ ተቋሙ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት ለሀገራዊ ፈጠራ መጎልበት፣ የኢኖቬሽን፣ ቴክኖሊጂ ሽግግር እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ማደግ ጥቅም ላይ የሚውልበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ሀገራዊ የመዋቅር ሽግግርን መደገፍ የሚል ተልዕኮ አንግቦ እየሠራ ይገኛል። የእስካሁኑ የንግድ ምልክት፣ ቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና የፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) ምዝገባ   የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ወርቅነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ2015 ዓ.ም እስከ ያዝነው በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ድረስ በንግድ ምልክት፣ በቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና በፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) 20 ሺህ 476 ምዝገባዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ 14 ሺህ 729 የንግድ ምልክቶች፣ 5 ሺህ 254 የቅጅና ተዛማጅ መብቶች እንዲሁም 1 ሺህ 781 የፈጠራ ሥራ ባለቤትነት ምዝገባ በተቋማችን አማካኝነት ተከናውኗል። የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች ምንድን ናቸው? አዕምሯዊ ንብረት ማለት በሰው ልጅ አዕምሮ የሚፈጠሩ የፈጠራ ሥራዎችን የሚመለከት መሆኑን የገለፁት አቶ ብሩክ፤ እነዚህ የፈጠራ ሥራዎች እንደማንኛውም ቁሳዊ ሀብት በንብረትነት የሚታወቁበትን አግባብ የያዘው ሥርዓት ደግሞ የአዕምሯዊ ንብረት መብት እንደሚሰኝ ያስረዳሉ። በዚህ አግባብ፤ የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች እንደማንኛውም ቁሳዊ ንብረት ሁሉ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ባለመብቶች የሚሰጡ የባለቤትነት መብቶች መሆናቸውን እንረዳለን። ለዚህም እንደ ምክንያት የሚቀርበው እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ ወጥ ሥራዎችን ለማመንጨት የፈጠራ ባለመብቶች ዕውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውንና ጊዜያቸውን መስዋዕት በማድረግ ከብዙ ድካም በኋላ ያገኟቸው የፈጠራ ውጤቶች በመሆናቸው ነው። ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ ለምን አስፈለገ? አንድም፤ የሰው ልጅ ቀጣይ ዕድገትና የኑሮ ደኅንነት ዋስትና መሠረት የሚያርፈው በቴክኖሎጂና ባሕል ዘርፎች በሚያሳርፋቸው ፈጠራዊ ብቃቶቹ በመሆኑ እንዲሁም የምርምርና የፈጠራ ሥራዎችን ለማካሄድ ተጨማሪ ሀብት የሚያስገኝ በመሆኑና ይህም የኢኖቬሽን ሥርዓቱን ስለሚያሳድግ ነው ይላሉ አቶ ብሩክ። እንዲሁም፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃና ዘርፉን ለሕዝብ የማስተዋወቅ ተግባር ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማረጋገጥ የድርሻውን ስለሚወጣና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት በአጠቃላይ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ በተሻለ ደረጃ ላይ እንዲቆም ስለሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም፤ ሀገራት ጠንካራ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠሩ ቁጥር ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ የልማት መሣሪያ መሆኑን ይገነዘባሉ። ጠንካራና ፍትሐዊ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠራ ባለቤቶችና በተጠቃሚው ሕዝብ ዘንድ ሚዛናዊ ነው ያሉት አቶ ብሩክ። በአጠቃላይ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን በአጽነዖት አንስተዋል። ዜጎች በአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት እንዴት ተጠቃሚ ይሆናሉ? ባለብዙ ቢሊየን ዶላር የፊልምና ድምጽ ሪከርድስ አሳታሚዎችና ሶፍትዌር ኢንዱስትሪዎች ለብዙ ሚሊየኖች የመዝናኛ ሥራዎች የሚያበረክቱት የቅጅ መብት ጥበቃ በመኖሩ መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አቶ ብሩክ ይናገራሉ። በሌላ በኩል ተጠቃሚዎች የሚፈልጓቸውን ምርቶችና አገልግሎቶችን መለየት የሚያስችላቸው ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ የንግድ ምልክቶች ጥበቃና የመብት ማስከበር ሥርዓቶች ባይኖሩ ኖሮ ተመሳስለው በሚቀርቡ ምርቶችና አገልግሎቶች መታለልና ሌሎችም ችግሮች ያጋጥማቸው እንደነበርም ጠቁመዋል። ስለዚህ ምርቶችን በመሸመት ሂደትም በምርቶችና አገልግሎቶች ላይ ያለምንም ግራ መጋባት ግብይቱን ማከናወን እንደሚያስችላቸው መገንዘብ ይቻላል። እንደ አቶ ብሩክ ገለጻ፤ ለፓተንት የፈጠራ ሥራዎች ጥበቃ በመደረጉ መሰጠት የሚገባቸው ማበረታቻዎች የማይሰጡ ከሆነ፤ የፈጠራ ባለሙያዎች ቀጣይ የምርምር ሥራዎችን ማሳደግና ማስፋት እንደማይችሉ ይገመታል። በቀጣይነት የሚገኙ የተሻሻሉ የፈጠራ ሥራዎች አለመኖራቸው ደግሞ፤ በምርቶች ተጠቃሚና አጠቃላይ የኑሮ መሻሻል ሂደት ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተፅዕኖ ይኖረዋል። የአዕምሯዊ ንብረት ዓይነቶች እንዴት ይመደባሉ? የአዕምሯዊ ንብረት፤ የኢንዱስትሪያዊ ንብረት (Industrial Property) እና የቅጅና ተዛማጅ መብቶች (Copyright and Related Rights) በሚሉ ሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚመደብ ያስረዳሉ። አክለውም፤ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት በውስጡ፤ የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ የኢንዱስትሪያዊ ንድፍ እና የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች የተሰኙ አራት ክፍሎችን እንደሚይዝ ያብራራሉ። ፓተንት ምንድን ነው?፡- ፓተንት ማለት በአንድ ቴክኒካዊ ባሕርይ ባለው የፈጠራ ሥራ ላይ የሚኖር የፈጠራ ባለቤትነት ብቸኛ መብት መሆኑን አቶ ብሩክ አስረድተዋል። የፓተንት መብት በአንድ ምርት (ለምሳሌ ማሽን ወይም የአመራረት ሂደት (Process) ሊሰጥ የሚችል ሲሆን፤ ፈጠራውም ለአንድ ቴክኒካዊ ችግር መፍትሔ የሚያስገኝ መሆን ይኖርበታል ይላሉ። ከፈጠራ ሥራው አመንጪ ይሁንታ ውጭ ሥራውን ገበያ ላይ ማዋል፣ መጠቀም፣ ማሰራጨት፣ መሸጥ ወዘተ… እንደማይቻልም አክለዋል። ፓተንት ለባለ መብቱ የጥበቃ መብት የሚያስገኝ ሲሆን፤ የጥበቃው ዘመንም በአጠቃላይ እስከ 20 ዓመት ሊደርስ ይችላል። ፓተንት የሚያስገኛቸው ሕጋዊ (የጥበቃ) መብቶች፡- የፈጠራ ሥራውን መጠቀም የሚችሉና የማይችሉ ሰዎችን መወሰን፤ ሦስተኛ ወገኖች ሥራውን እንዲጠቀሙ የመፍቀድ ወይም የፈቃድ ውል ስምምነት የመስጠት እንዲሁም የፈጠራ ሥራውን የመሸጥ (ለአዲስ የፓተንት ባለመብት) የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል ሥራ አስፈጻሚው። የፓተንት ሥራዎች ለምን ያስፈልጋሉ?፡- ይህን ሲያብራሩም፤ ፓተንት ለፈጠራ ባለመብቶች ዕውቅናንና ሽልማቶችን (ማበረታቻዎችን) የሚሰጥ በመሆኑ፣ ፈጠራዎቹ የኢኖቬሽን ሥራዎችን ስለሚያጠናክሩና በዚህም ቀጣይነት ያለው የሰው ልጅ ሕይወት መሻሻልን የሚያረጋግጥ በመሆኑ እና በሌሎችም በጎ አስተዋጽዖዎች ፓተንት በዕጅጉ አስፈላጊ ነው ብለዋል። የንግድ ምልክት ምንድን ነው?፡- የንግድ ምልክት ማለት አንድን ምርት ወይም አገልግሎት ከሌላው ምርትና አገልግሎት እንዲለይ ለማስቻል በንግድ ምልክት ባለቤቶች ለምርታቸውና አገልግሎታቸው መለያ እንዲሆን ጥቅም ላይ የሚውል ልዩ ምልክት መሆኑን ተናግረዋል። የንግድ ምልክት ሸማቹ ሕብረተሰብ የሚፈልገውን ምርትና አገልግሎት በቀላሉ ለይቶ እንዲገዛ ከማስቻሉም በላይ በሚገዛው ምርትና አገልግሎት ጥራት ላይ በመተማመን ፍላጎቱን እንዲያሟላ ያደርጋል። የንግድ ምልክት ለባለመብቱ ምን ጥቅም ያስገኛል?፡- ምርቶቹ (አገልግሎቶቹ) በተጠቃሚዎች እንዲለዩለት ወይም እንዲታወቁለት ያደርጋል፣ ክፍያን መሠረት አድርጎ ሦስተኛ ወገን እንዲጠቀምበት የመፍቀድ፣ የንግድ ምልክቶች በራሳቸው ዋጋ አላቸው (የአዕምሯዊ ንብረት ዋጋ ትመና (IP Valuation) ለምሳሌ በፈረንጆቹ በ2026 የመጀመሪያ ወራት አፕል (Apple) 600 ቢሊየን ዶላር፣ ማይክሮሶፍት (Microsoft) 565 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር፣ ጉግል (Google) 433 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ዋጋ ግምት እንደነበራቸው ተብራርቷል። በተጨማሪም፤ የንግድ ምልክት በሕግ በሚቀመጥ የጊዜ ገደብ መሠረት እየታደሠ ለዘላለም ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል፤ የንግድ ምልክት ባለቤቱን በማስተዋወቅ ዕውቅናና የገንዘብ ትርፍን ያስገኛል፤ የንግድ ምልክት ተገቢ ያልሆኑ የንግድ ውድድሮችን በመግታት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል (ተመሳስለው የሚሠሩና ለገበያ የሚቀርቡ ሥራዎችን (Counterfieited Products) ለመዋጋት ዓይነተኛ መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል፤ የንግድ ምልክት ሰዎች ምርቶቻቸውንና አገልግሎቶቻቸውን ሚዛናዊ በሆነ አግባብ እንዲያቀርቡ በማድረግና በብሔራዊና ዓለም አቀፍ ደረጃ የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት እንዲኖር ምቹ ሁኔታ በመፍጠር አስተዋጽዖው የላቀ ነው ብለዋል። ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ምንድን ነው?፡- ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ በምርቶች ሥነ-ውበት (Esthetics) ላይ ተመስርቶ ቅርጽን፣ መስመሮችን ወይም ቀለምን በመጠቀም ለገበያ የሚቀርቡ ምርቶች የገዥዎችን (ሸማቾችን) ቀልብ ለመሳብ እንዲችሉ በምርቶች ላይ የሚገለጽ የንድፍ ጥበብ ዘርፍ ነው ያሉት አቶ ብሩክ፤ ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች በኢንዱስትሪና ዕደ-ጥበብ ምርቶች ላይ ተዘጋጅተው ሊወጡና ለገበያ ሊቀርቡ ይችላሉ ይላሉ። ዘርፉ ከቴክኒካልና ሕክምና መሣሪያዎች አንስቶ እንደ ሠዓት፣ ጌጣጌጦችና ሌሎች የቅንጦት ምርቶች ዕቃዎችን ሊያካትት ይችላልም ብለዋል። የቤት ዕቃዎችን፣ የኤሌክትሪክ መሣሪያዎችን፣ ተሽከርካሪዎችና የሕንጻ ንድፎችን እንዲሁም የጨርቃጨርቅ ንድፍ ውጤቶች በኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ሥር የሚወድቁ ይሆናሉ ይላሉ። ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች ጥበቃ የሚደረግላቸው አዲስ ወይም ወጥ ከሆኑ ብቻ መሆኑን ገልጸው፤ በዲዛይኑ ውስጥ ከሚገለጸው ምርት ጋር ተያያዥ የሆኑ የቴክኒክ ጉዳዮች ጥበቃ እንደማይደረግላቸው አስታውቀዋል። ለኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ጥበቃ ማድረግ ለምን ያስፈልጋል?፡- በምርቶች ውበት ላይ የሚገለጽ በመሆኑ የተጠቃሚውን ዐይን ይስባል፣ የምርቶችን ዋጋ ይጨምራል፣ ፈጠራንና ውድድርን ያበረታታል፣ ለባለመብቱ ብቸኛ መብትን ያጎናጽፋል፣ በኢንዱስትሪዎች፣ ባሕላዊ ጥበብና በዕደ ጥበብ ዘርፍ ፈጠራ በማሻሻል ኢኮኖሚ እንዲያድግ ያደርጋል፣ የወጭ ንግድን (Export Trade) ያሳድጋል በማለት የኢንዱስትሪ ንድፍ ጥበቃ አስፈላጊነትን ያብራራሉ። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካች ምንድን ነው?፡- የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች በምርቶች ላይ የሚቀርቡ ምልክቶች ሆነው እነዚህ ምልክቶች አንድ የተወሰነ አካባቢን በምርቱ ምንጭነት የሚያመላክቱና ጥራትንና ዝናን ከቦታው ጋር አስተሳስረው የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን አቶ ብሩክ ያስረዳሉ። በአብዛኛው የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች ልዩ ምርቱ የሚገኝበትን የቦታ ስም (Specific Local Geographyical Factors – Climate, Soil) ይይዛሉ። ለምሳሌ፡- Roquefort for Cheese -France፣ የማረቆ በርበሬ፣ የሸኖ ቅቤ፣ የዓድኣ ጤፍ … የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሾች ናቸው። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾችን መጠበቅ ለምን ያስፈልጋል?፡- ተጠቃሚዎች ምርቶች የሚገኙበትን ሀገር ወይም አካባቢ በቀላሉ ለመለየት፣ ሕጋዊነት በሌላቸው ወገኖች የምርቱ መገኛ አካባቢ እና የምርቱ ዝና በተሳሳተ መልኩ ለሌላ ምርት መጠሪያ እንዳይውል ለመከላከል ይረዳል ይላሉ። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምንድን ናቸው?፡- የቅጅ መብት በሥነ-ጽሑፍ እና ሥነ-ጥበብ ዘርፍ ወጥ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ደራስያን፣ አርቲስቶች ወዘተ… የባለቤትነት መብት የሚሰጥ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑንም ነው ሥራ አስፈጻሚው የሚያስረዱት። በአንጻሩ ተዛማጅ የቅጅ መብት ማለት ይላሉ አቶ ብሩክ፤ በወጥ የፈጠራ ሥራዎች ላይ ተመስርተው የሚሠሩ ተዛማጅ (Related) የፈጠራ ሥራዎችን ያካትታል። ለምሳሌ፡- ከዋኞቹ (ተዋንያን እና ዘፋኞች)፣ ድምጽ ሪከርዲንግስ፣ አሳታሚዎች (ኮምፓክት ዲስኮች)፣ የብሮድካስት ተቋማት፣ (ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን) የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ዘርዝረዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምን ዓይነት መብቶች ያስገኛሉ?፡- ባለመብቶች ሥራዎቻቸውን ለመጠቀም ወይም ሦስተኛ ወገኖች እንዲጠቀሙባቸው የመፍቀድ፣ ሥራዎች እንዲባዙ፣ ለሕዝብ እንዲዳረሱ፣ እንዲሠራጩ፣ እንዲተረጎሙ ወይም ወደሌላ ሥራ እንዲቀየሩ የመፍቀድ ወይም የመከልከል፣ የደራሲነት (የአመንጭነት) መብት ዕውቅና እንዲያገኙ፣ በብዕር ስም የመጠቀም መብት፣ ክብሩንና መልካም ስሙን የሚያጎድፍ የሥራ መዛባት እንዳይኖር የመጠበቅ ወይም የሥራው ወደሌላ መቀየር የሚያስከትለውን ጉዳት የመቃወም ወዘተ መብቶችን ያስገኛሉ ብለዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ምን ጥቅሞች ያስገኛል?፡- የሰውን ልጅ የፈጠራና ኢኖቬሽን ጥረቶችን ያሳድጋል፣ ለፈጠራ አመንጭዎች መበረታታትን ይፈጥራል፣ የሕጋዊ ተፈጻሚነትን በማረጋገጥ አመንጭዎችና በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች መዋዕለ-ነዋይ እንዲያፈሱ የፈጠራ ሥራዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚኖራቸውን የሥርጭት ሽፋን ያሳድጋል ነው ያሉት አቶ ብሩክ። የፓሪስ ስምምነት አባል ኢትዮጵያ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር ለመሆን ለዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት (WIPO) ያስገባችው ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስምምነቱን ነሐሴ 9 ቀን 2017 ዓ.ም በማጽደቁ ከዚሁ ዕለት ጀምሮ ለስምምነቱ ተገዢ ሆናለች። አቶ ብሩክ እንዳብራሩት፤ የፓሪስ ስምምነት በጥቅሉ የኢንዱስትሪያዊ ንብረቶችን ጥበቃ የሚመለከት ነው። የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ፣ የግልጋሎት ሞዴል (በአንዳንድ ሀገራት ሕግ ኢትዮጵያን ጨምሮ “የአነስተኛ ፈጠራ የባለቤትነት መብት” በመባል የተደነገገ)፣ የአገልግሎት ምልክት፣ የንግድ ስም (የኢንዱስትሪ ወይም የንግድ እንቅስቃሴ የሚካሄድባቸው ስያሜዎች)፣ ጂኦግራፊያዊ አመላካች እና ፍትሐዊ ያልሆነ ውድድርን መከላከል ያካተተ ነው። የስምምነቱ መሠረታዊ ድንጋጌዎች በሦስት ዋና ዋና መርሆዎች እንደሚከፈሉ ጠቁመው፤ እነሱም፡- የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር መሆን በሌሎች አባል ሀገራት ውስጥ እንደ ዜጋ የመስተናገድ መብት፣ የቀዳሚነት መብት የማግኘት፣ በቀላሉ ዓለም አቀፍ ጥበቃ የማግኘት አሠራር እና መሰል ጉልህ ጥቅሞችን የማግኘት ዕድል ይሰጣል ሲሉ ይገልጻሉ። በመሠረቱ የፓሪስ ስምምነት የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃን በማቀላጠፍ አዳዲስ ግኝቶችንና ፈጠራዎችን እንዲሁም የንግድ ሥራዎች ድንበር ሳይገድባቸው የፓተንትና የንግድ ምልክት መብቶች በቀላሉ እንዲጠበቁ በማድረግ ፈጠራን፣ ንግድን እና ኢኮኖሚያዊ እድገትን እውን ያደርጋል ብለዋል። የዘንድሮው የአዕምሯዊ ንብረት ቀን የፊታችን ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም “አዕምሯዊ ንብረትና ስፖርት፤ እንዘጋጅ፣ እንጀምር፣ እንፍጠር!” በሚል መሪ ሐሳብ ዓለም አቀፉ የአዕምሯዊ ንብረት ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል። በስፖርት ዓለም ውስጥ የሚከሰቱ ተወዳዳሪዎች የግልና የጋራ ፈጠራዎች፣ ንድፎች፣ ብራንዶችና የመልካም ዝና ታሪኮችን ለመጠበቅና ሀገራትን ጭምር ለማስተዋወቅ የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃ ሥርዓት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል። ምክንያቱም ስፖርት በባሕርይው በውድድር ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን፤ ከሀገራት ዝና፣ ከፋሽን ዲዛይን፣ ከመዝናኛ፣ ከሚዲያ ሥርጭት፣ ከጤናና ከዕለት ተዕለት መገልገያ ቁሶች ጋር የሚገናኝ በመሆኑ ነው።  
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 943
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ ‎በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ‎ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
የንፋስ ኃይል፤ የኢትዮጵያ የብርሃን አድማስ የአረንጓዴ ልማት ሌላኛው ብስራት!!
Apr 18, 2026 151
በቁምልኝ አያሌው የሰው ልጅ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን መጠቀም የጀመረው በጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዘመን እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። ለአብነትም፤ ግብፃውያን ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት ጀልባዎችን በባሕር ላይ ለመንዳት የንፋስ ኃይልን ይጠቀሙ ነበር። በሰባተኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ደግሞ ፋርስ (የአሁኗ ኢራን) የመጀመሪያውን በንፋስ ኃይል የሚሠራ የጥራጥሬ መፍጫ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ ማዋል ጀመረች። ግሪኮችና ሮማውያን የውሃ መንኮራኩሮችን በመጠቀም እህል መፍጨት የሚያስችል ፈጠራን እንዳስጀመሩ የታዳሽ ኃይል የታሪክ ማኅደሮች ይጠቁማሉ። ጥንታዊያን ሕዝቦች የፀሐይ ኃይልን ለብርሃንና ለሙቀት ምንጭነት ከመጠቀም ባለፈ፣ የፀሐይ ጨረርን በማሰባሰብ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚጠቀሙባቸውን ጥበቦች ነበሯቸው። ምንም እንኳን የ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢንዱስትሪ አብዮት በድንጋይ ከሰልና በተፈጥሮ ዘይት የበላይነት ቢያዝም፤ በዚሁ ወቅት ለታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ልማት መሠረት መጣሉን ታሪክ ያስትውሰናል። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው እ.አ.አ በ1839 ፈረንሳዊ የፊዚክስ ሊቅ ኤድመንድ ቤኩረል፤ የፀሐይ ብርሃንን ወደ ኤሌክትሪክ መቀየር የሚቻልበትን የ'ፎቶቮልታይክ' (Photovoltaic effect) ክስተት ማገኘቱ ነው። በተጨማሪም እ.አ.አ በ1882 የመጀመሪያው በውሃ ኃይል የሚሰራ የኤሌክትሪክ ማመንጫ በአሜሪካ ሥራ ጀመረ። እ.አ.አ በ1883 ደግሞ በኦስትሪያ ቪየና በተካሄደው ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ኤግዚቢሽን፣ የንፋስ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ የሚቀይሩ ተርባይኖችን ለመትከል የሚያስችሉ ወሳኝ የቴክኖሎጂ ዕድሎች ታይተዋል። በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ለታዳሽ ኃይል የሚሰጠው ትኩረት መቀዛቀዝ ቢያሳይም፣ በ1970ዎቹ የተከሰተው ዓለም አቀፍ የነዳጅ እጥረት ዓለም አማራጮችን እንድታማትር አስገድዷታል። በዚህም ምክንያት የነዳጅ ዋጋ መናር ሀገራት ከነዳጅ ጥገኝነት ለመውጣት ወደ ውሃ፣ ፀሐይና ንፋስ ኃይል ፊታቸውን እንዲያዞሩና በዘርፉ ለሚካሄድ ጥናትና ምርምር ከፍተኛ መነሳሳት እንዲፈጠር አድርጓል። የንፋስ ኃይል ታሪካዊ ዳራና የቴክኖሎጂ እድገት የንፋስ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ የመቀየር ታሪክ እ.አ.አ በ1883 በኦስትሪያ ቪየና በተካሄደው ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ኤግዚቢሽን ላይ ፍሬድላንድ በተሰኙ ሳይንቲስት አማካኝነት የመጀመሪያው የንፋስ ኤሌክትሪክ ተርባይን ለእይታ መቅረቡ ይነገራል። ይህ የፈጠራ ሥራ በየጊዜው እየተሻሻለ መጥቷል። በ1887 ስኮትላንዳዊው የኮሌጅ ፕሮፌሰር ጄምስ ብሊዝ የቤታቸውን መብራት ለማብራት የተጠቀሙበት የንፋስ ተርባይን በዘርፉ ትልቅ እመርታ ተደርጎ ይወሰዳል። ፕሮፌሰሩ ቀስ በቀስ የፈጠራ ውጤታቸውን አሳድገዋል። የአካባቢው ማኅበረሰብም የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ እንዲሆን ያቸሉትን አድርገዋል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታ በበርካታ ሀገራት የተለያዩ ሙከራዎች መደረጉን ድርሳናት ሲፈተሹ የሚያሳዩት እውነት ነው። ሆኖም ዘርፉ ትኩረት አግኝቶ እንዲያድግ ያደረገው በ1973 በዓለም ላይ የተከሰተው የነዳጅ ቀውስ ነው። ይህ ክስተት ሀገራት ወደ አማራጭ ኃይል ምንጮች እንዲያተኩሩ ዕድል ፈጥሮላቸዋል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ መጠነ ሰፊ የንፋስ ኃይል እርሻዎችን (Wind Farms) በመገንባት ግንባር ቀደም መሆን ችላለች። እ.አ.አ እስከ 2008 ድረስ ከዘርፉ የምታመነጨውን የኃይል መጠን ወደ 24.4 ጊጋ ዋት አሳድጋለች። የንፋስ ኃይል የማመንጨት ሂደት የንፋስን የተፈጥሮ እንቅስቃሴ በተርባይኖች አማካኝነት ወደ ሜካኒካዊ ኃይል፣ በመቀጠልም ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚቀይር ዘመናዊ የታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ነው። ሂደቱም የተርባይን ክንፎች በንፋስ ግፊት አማካኝነት በሚፈጥሩት ሽክርክሪት ጀኔሬተሩን በማንቀሳቀስ ኤሌክትሪክ እንዲመነጭ ያደርጋል። የዓለማችን ግዙፍ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች የት ይገኛሉ? በአሁኑ ወቅት በዓለማችን ከ350 ሺህ በላይ የንፋስ ተርባይኖች ተተክለው ኃይል እየሰጡ ይገኛል። ቻይና በንፋስ ኃይል ማመንጨት የዓለማችን ቀዳሚ ሀገር ስትሆን፤ አሜሪካ እና ጀርመን በቅደም ተከተል ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። የቻይናው ጂኳን (Gansu) የንፋስ ኃይል ማመንጫም ከ20,000 ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ያለ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው። የንፋስ ኃይል በኢትዮጵያ ዓለም ለታዳሽ ኃይል ልማት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ የንፋስ ኃይል ልማት ቀዳሚ ተዋናይ የሚያደርጋትን ስራዎች እያከናወነች ነው። ሀገሪቷ በምስራቅ አፍሪካ ያላት ስትራቴጂካዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ የታደለችውን የተፈጥሮ ፀጋ ወደ አማራጭ ኃይል ለመቀየር ሰፊ ዕድል ፈጥሮላታል። በንፋስ ኃይል ልማት የመጣው ከፍተኛ ለውጥም የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፍላጎትን በመሙላት የብዝኅ ታዳሽ ኃይል አማራጭ ልማት እንዲጎለብት እያደረገ ይገኛል። የተፈጥሮ ስጦታና ያልተነካው የኢትዮጵያ እምቅ የንፋስ ኃይል ፀጋ ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አኳያ በንፋስ ኃይል አማራጭ እምቅ የመልማት ፀጋን ተችሯታል። በተለይም የታላቁ ስምጥ ሸለቆ፣ ሰሜናዊ ተራራማ ስፍራዎችና ምስራቃዊ ቆላማ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የንፋስ ፍጥነት ኃይልን ለማመንጨት ተስማሚ መልክዓ ምድሮች ናቸው። በዚህም ኢትዮጵያ እስከ አንድ ነጥብ ሦስት ሚሊዮን ሜጋ ዋት የንፋስ ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይህ አሃዛዊ መረጃም ከአሁኑ ወቅት አጠቃላይ ኃይል የማመንጨት አቅም ጋር ሲነፃጸር ሰፊ የልማት ዕድል መኖሩን ያረጋግጣል። ከጅምር እስከ ዛሬ የስኬት ጉዞ ምዕራፍ የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት በ2001 ዓ.ም አሸጎዳ ፕሮጀክት ግንባታ ተጀምሯል። በአዳማ 1 እና 2 ስራውን በማስፋት አሁን ላይ እስከ አይሻ 1 እና አሰላ ፕሮጀክቶች ደርሷል። እነዚህ የአዳማ፣ የአሸጎዳ፣ የአይሻ እና የአሰላ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል አድማስ መስፋፋትን የሚያረጋግጡ ናቸው። ለሀገሪቷ አረንጓዴ ልማት ብስራት የሆኑ ታላላቅ ስራዎች ናቸው። አዳማ-1 እና ሁለት፡- በአጠቃላይ 204 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው የአዳማ የኤሌከትሪክ ማመንጫዎች የኢትዮጵያን የንፋስ ኃይል የማመንጨት አቅም በተግባር ያረጋገጡ ፋና ወጊዎች ናቸው። አሸጎዳ፡- በፈረንሳይ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ የተገነባ ሁለተኛው የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ነው። 120 ሜጋ ዋት የሚያመነጨው ይህ ጣቢያ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሚገኙ ዜጎች ከሚሰጠው ብርሃን በተጨማሪ የኢንዱስትሪ አቅም ሆኗል። አይሻ-2፡- በቅርቡ ተመርቆ ወደ ስራ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 80 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል። በኢትዮ-ጅቡቲ ድንበር አቅራቢያ መገናባቱም ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው። አሰላ፡- በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን የምትገኝ የኢትዮጵያ ብርቅየ አትሌቶች መፍለቂያ ስፍራ ናት። በስንዴና ገብስ የግብርና ምርታማነትም በተምሳሌትነት ትጠቀሳለች። ነፋሻማ የአየር ሁኔታዋም ለኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አቅም የሚሆን ፀጋን ተችሯታል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ 08 ቀን 2018 ዓ.ም 100 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚያስችለውን የአሰላ ንፋስ ኃይል መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም አርሲ በስንዴና ገብስ ብቻ ሳይሆን በንፋስ ኃይልም የኢትዮጵያ ብልፅግና ማዕከል መሆኗን የአካባቢውን የብዝኅ ፀጋ አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም ኢትዮጵያ ከዕዳና ኪሳራ ወጥታ ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜ ማጠናቀቅና ማትረፍ መጀመሯን በተግባር ያሳየ ነው። ከዚህም በላይ በንፋስ እና በጂኦተርማል ኃይል ማመንጫዎች የኢነርጂ ማዕከል እየሆነ መምጣቷን ያረጋግጣል። "አርሲ በኃይል ዘርፍ ልክ እንደ ስንዴ እና ገብስ ተጨማሪ አቅም ያለው አካባቢ መሆኑን ማየት ችለናል" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በንግግራቸው። የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ በ145 ሚሊዮን ዩሮ ወጪ የተገነባ መሆኑን በመጥቀስ፤ ፕሮጀክቱ በአዋጭነት ደረጃ ሲታይ እጅግ ስኬታማ ነው ብለዋል። ከዚህ ቀደም የሚወሰዱ ብድሮች ለትውልድ ዕዳ ትተው የሚያልፉ እንደነበሩ በማስታወስ፣ የአሁኑን ፕሮጀክት የተለየ የሚያደርገውን ነጥብ ሲያነሱ ይህ ፕሮጀክት ቢበዛ በሁለት ዓመት ሙሉ ወጪውን ሸፍኖ ትርፋማ ስለሚሆን ልጆቻችን ትርፍ ሀብት የሚያገኙ እንጂ ዕዳ የሚረከቡ አይሆኑም በማለት ነው የገለጹት። ፕሮጀክቱ እውን እንዲሆን ግማሹን በእርዳታ እንዲሁም ቀሪውን ከወለድ ነጻ በሆነ ብድር ላቀረበችው የዴንማርክ መንግሥት የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱም ቢበዛ በሁለት ዓመት ሙሉ ወጪውን ሸፍኖ ትርፋማ ስለሚሆን ልጆቻችን ምንዳ እንጂ ዕዳ የሚረከቡ እንደማይሆን አስገንዝበዋል። በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ ላይ በደማቅ ሁኔታ የተመረቀው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት የጀመረችውን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ሌላኛው ታሪካዊ አሻራ ነው። በመደመር መንግስት መፅሐፍ ገፅ 206 ላይ እንደተጠቀሰው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋት ባለፉት ዓመታት ሰፊ ኢንቨስትመንት ተካሂዷል። ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትም ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷል። የታላቁ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫን ጨምሮ ሌሎች በጅምር ያሉና በሚገባ አገልግሎት እየሰጡ ያልነበሩ ማመንጫዎችን ወደ መስመር ለማስገባት ተችሏል። በዚህም ሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚያስፈልጋትን የኃይል አቅርቦት በሚገባ መሸፈን ችለናል በማለት ተከትቧል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 504 ሜጋ ዋት ኃይል ብሔራዊ የኃይል ቋትን በመመገብ የኃይል አቅርቦት የጀርባ አጥንት ሆነዋል። በኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ቀደም ሲል የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በመንግስት ብቸኛ ይዞታነት ብቻ ሲካናወኑ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት ግን ይህን አሰራር የሚቀይር የፖሊሲ ማሻሻያ ተደርጓል። ባለሃብቶች በመንግስትና የግል አጋርነት (PPP) ማዕቀፍ የሚሳተፉበት ሰፊ ዕድል ለመፍጠር ተችሏል። ይህም የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ከማበረታታቱም በላይ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የግሉን ዘርፍ በኃይል ልማት ላይ ለማሳተፍ የተወሰዱት የፖሊሲ እርምጃዎች አሁን ላይ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ጀምረዋል። ለአብነትም፤ በሶማሌ ክልል በመንግስትና በግል አጋርነት የሚገነባው የአይሻ-1 እና 3 የንፋስ ኃይል ፕሮጀክት ከ300 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን ባለፈ፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለውን የኃይል ትስስር በማጠናከር ለጋራ ዕድገት መፋጠን ጉልህ ፋይዳ አለው። ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ በመገንባትና የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቀነስ ረገድ የምትከተለው የልማት መንገድ ለሌሎች ሀገራትም ተምሳሌት የሚሆን ነው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ከብርሃን ባሻገር የንፋስ ኃይል የኢትዮጵያን የኃይል አቅርቦት በማሟላት ለሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ስትራቴጂክ መሰረት እየጣለ ይገኛል። ለአብነትም በኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ እያበረከተ ያለውን ፋይዳ መጥቀስ ይቻላል። የኢነርጂ ዋስትና እና የኃይል ምንጭ ስብጥር፡- በኢትዮጵያ ከውሃ ኃይል የማመንጨት ተግባር ቀዳሚውን ድርሻ ይይዛል። ይህም በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በሚከሰት የድርቅ አደጋ የኃይል አቅርቦት ተጋላጭነት በማስፋት ተፅዕኖ ያሳድራል። የንፋስ ኃይልም የአቅርቦት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ጉልህ ስትራቴጂክ ፋይዳ አለው። በበጋ ወራት የውሃ መጠን ሲቀንስ የንፋስ ኃይልን በመጠቀም ደግሞ የተፈጥሮ ሚዛንን የጠበቀ አስተማማኝ የኃይል ስብጥር ለመገንባት ጉልህ ፋይዳ ያበረክታል። የኢንዱስትሪ መፋጠንና የሥራ ዕድል፡- የኃይል አቅርቦት ለአስተማማኝ የኢንዱስትሪ ምርታማነት የጀርባ አጥንት ነው። የኢንዱስትሪው ዘርፍ ደግሞ ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ሚና አለው። በተለይም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገነቡ የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶች የዕውቀትና የምርታማነት ሽግግርን በማፋጠን ረገድ ፋይዳቸው የጎላ ነው። እነዚህ ፕሮጀክቶች በንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ተከላና ጥገና ወቅት የዜጎችን የምህንድስና ክህሎት በማጎልበት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግሩን በተጨባጭ ያጠናክራሉ። ፋብሪካዎች አስተማማኝ ኃይል እንዲያገኙ በማድረግ የገቢ ምርቶችን የመተካትና የወጪ ንግድ አቅማቸውን በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ። ቀጣናዊ ትስስርና የውጭ ምንዛሬ ግኝት፡- የኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከልነት አቅም የሚያጎለብቱ ከአነስተኛ እስከ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል፤ በመገንባታ ሂደትም ናቸው። የንፋስ ኃይል ልማትም ቀጣናው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን እየደገፈ ይገኛል። ይህም የዕድገት ትስስርን በማፋጠን በየዓመቱ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያበረክታል። የአረንጓዴ አሻራና የአካባቢ ጥበቃ፡- የንፋስ ኃይል ከብክለት የፀዳ ንፁህ የኃይል ምንጭ ነው። ይህም ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት የተቸራትን ዓለም አቀፍ ዕውቅና ለማፅናት በቀላሉ አይታይም። የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ የፋይናንስ ገቢን በማሳደግም ተጨማሪ የታዳሽ ኃይል ልማትን ለማጠናከር ያስቻላል። የገጠሩን ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚነት በማስፋትም የአካባቢና የደን መራቆትን ለመቀነስ ያስቻል። የንፋስ ኃይል ልማት ለኢትዮጵያ ቅንጦት አይደለም፤ ይልቁንስ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ዕድገትን የማፋጠን የህልውና ጉዳይ ነው። ለዚህም የንፋስ ኃይል ፀጋዎችን በማልማት ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የንፁህ ኢኮኖሚ ግንባታ ፋና ወጊነት የሚያረጋግጥ የልማት አቅጣጫ ተተልሞ እየተሰራበት ነው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማትም አዲስ ተስፋን የፈነጠቀ የብርሃን አድማስና የአረንጓዴ ልማት ሌላኛው ብስራት እየሆነ ይገኛል።  
በፈተናዎች ሁሉ የጸናው የኢትዮጵያና የላይቤሪያ ወዳጅነት
Apr 14, 2026 1185
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያና ላይቤሪያ ዘመናትን የተሻገረ ወዳጅነት አላቸው። ይሄ ወዳጅነት በፈተናዎች ጊዜ ሁሉ ጸንቶ የዘለቀም ነው። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ውስጥ ብቸኛ ነፃ ሀገራት በመሆናቸው፣ በዓለም አቀፍ መድረኮች (ለምሳሌ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ) የአፍሪካውያን ድምፅ ሆነው በጋራ ይቆሙም ነበር። የሀገራቱ የወዳጅነት እና የትብብር ስምምነትም እ.አ.አ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ የጀመረ ሲሆን፣ በመካከላቸው ያለው ዘላቂ ወዳጅነት እና በዓለም አቀፍ መድረኮች (እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት) በጋራ ለመቆም ቃል የተገባበት ሰነድም ተደርጎ ይወሰዳል። የዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሠረት የጣሉትም ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እና ፕሬዝዳንት ዊሊያም ቱብማን ናቸው። እ.ኤ.አ. በ1954 ፕሬዝዳንት ቱብማን ወደ አዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ይፋዊ ግንኙነት እንዲጀመር በር ከፍቷል። ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እ.አ.አ. 1958 ጉብኝት ወደ ሞንሮቪያ በማድረግ፣ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኙ የነፃነት ንቅናቄዎችን በጋራ ለመደገፍ ተወያይተዋል። እነዚህ ጉብኝቶች የሁለትዮሽ ብቻ ሳይሆኑ አህጉራዊ ፋይዳም ነበራቸው። እ.አ.አ በ1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ሲመሰረት፣ ሁለቱ ሀገራት "የሞንሮቪያ" እና "የካዛብላንካ" ቡድኖችን ልዩነት በውይይት በመፍታት ለአህጉሪቱ አንድነት የጀርባ አጥንት መሆናቸውን አስመስክረዋል። በ1960ዎቹ መጀመሪያ ላይ በ”ሞንሮቪያ ቡድን” እና "የካዛብላንካ ቡድን" መካከል የነበረውን ልዩነት ለማጥበብ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በጋራ በመስራታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሊመሰረት ችሏል። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በችግር ውስጥ የተፈተነ ወዳጅነት ነው የሚል ሀሳብ በብዙዎች ይነሳል። የዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ በላይቤሪያ የነበራት የሰላም ማስከበር ሚና ነው። ላይቤሪያ ለ14 ዓመታት በዘለቀው አውዳሚ የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት መንግሥታዊ መዋቅሯ ፈርሶ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2003 የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ሰላም እንዲያስከብሩ ከጠራቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ ነበረች። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ በርካታ ሰራዊቷን በማሰማራት ለሀገሪቷ ሰላም ዋጋ ከፍላለች። ሰራዊቱ አማፂያንን ትጥቅ በማስፈታት፣ ተዋጊዎች ከማህበረሰብ ጋር እንዲቀላቀሉ በማድረግ እና የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ከፍተኛ ስራ ሰርቷል። ዋና ከተማዋ ሞንሮቪያ እና በገጠራማ አካባቢዎች የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንዳይጣስ ጥብቅ ቁጥጥር አድርጓል። የኢትዮጵያ ሰራዊት የጤና ቡድን በየሰፈሩ በመዘዋወር ለላይቤሪያውያን ነፃ የህክምና እርዳታ እና መድሃኒትም ይሰጥ ነበር። ሰራዊቱ የራሱን ስንቅ ለተቸሩ ዜጎች በማካፈል ወንድማማችነትን በተግባር አሳይቷል። እ.ኤ.አ በ2014 የኢቦላ ወረርሽኝ በላይቤሪያ በከፋ ሁኔታ በተከሰተበት ወቅትም፣ ሌሎች ሀገራት ሰራዊታቸውን ሲያስወጡ ኢትዮጵያ ግን የህክምና ቡድኖችን እና ሰራዊቷን በማቆየት ከላይቤሪያ ህዝብ ጎን ቆማች። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ ሶስት ተከታታይ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫዎች እንዲካሄዱ በሰላም ማስከበሩ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የላይቤሪያ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች የላቀ አገልግሎት ሜዳሊያ እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ የነበራት የሰላም ማስከበር ሚና ከወታደራዊ ተልዕኮ ባለፈ የደም እና የአጥንት መስዋዕትነት ከፍላለች። ይህ የሰራዊቱ ተሳትፎ ዛሬም ድረስ በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ላለው ጥብቅ ወዳጅነት ዋነኛው ምክንያት ተደርጎ ይወሳል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራቱ መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች ለሁለትዮሽ ትብብሩ መጠናከር አስተዋጽኦ አድርገዋል። የቀድሞዋ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ እ.አ.አ በ2006 ስልጣን በያዙ ማግስት አዲስ አበባን ጎብኝተዋል። ይህም ኢትዮጵያ በላይቤሪያ ሰላም ለማስፈን ላደረገችው ድጋፍ እውቅና የሰጡበት ነበር። ሰርሊፍ በላይቤሪያ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ሲያበቃ እ.አ.አ ጁላይ 2015 ኢትዮጵያን በመጎብኘት ለተደረገላቸው የህክምና ቡድን ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። የቀድሞዋ ፕሬዝዳንት እ.አ.አ በ2017 ለሶስት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳላኝ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ፕሬዝዳንቷ በወቅቱ የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክን የጎበኙ ሲሆን ላይቤሪያ ከኢትዮጵያ የጨርቃ ጨርቅ ልማት ዘርፍ ልምድ መቅሰም እንደምትፈልግ በወቅቱ ገልጸው ነበር። የላይቤሪያ የእግር ኳስ ኮከብ እና የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ እ.አ.አ በ2018 ስልጣን ከያዙ በኋላ በአዲስ አበባ በተካሄደው 30ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የተሳተፉ ሲሆን ከጉባኤው ጎን ለጎን ከወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ተገናኝተው በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ተወያይተዋል። የቀድሞው የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲ-ማክስዌል ሳህ ከማያህ እ.አ.አ በ2022 በአዲስ አበባ ጉብኝት በማድረግ በሁለቱ ሀገራት መካከል የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን (Joint Ministerial Commission) እንዲቋቋም ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በላይቤሪያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (UNMIL) ላይ በነበረበት ወቅት፣ የተለያዩ የመከላከያ ሚኒስትሮች እና የጦር አዛዦች የኢትዮጵያን ሰላም አስከባሪ ኃይል ለመጎብኘት እና ከላይቤሪያ ባለስልጣናት ጋር ለመወያየት በተደጋጋሚ ወደ ሞንሮቪያ ተጉዘዋል። ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ውይይቶች በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነቶችም ተፈራርመዋል። ሰላም ፣ ደህንነት፣ ጤና፣ የአየር አገልግሎት፣ የቪዛ ነፃ መብት ፣ የንግድ ትብብር ማዕቀፍ፣ ግብርና፣ ትምህርት፣ ባህል እና ስፖርት ስምምነት ከተደረገባቸው ዘርፎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአየር አገልግሎት ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞንሮቪያ ያለምንም ገደብ እንዲበር እና ላይቤሪያን ከቀሪው ዓለም ጋር ማገናኘት የሚያስችል ህጋዊ ማዕቀፍ ነው። የሰላም ማስከበር ስምምነቱ በተባበሩት መንግሥታት ማዕቀፍ ውስጥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል እንድትልክ የተደረገው ስምምነት በላይቤሪያ መረጋጋት እንዲመጣ ትልቅ ድርሻ ነበረው። በኪነ-ጥበብ እና በስፖርት ዘርፍ (በተለይም በእግር ኳስ) የሁለቱ ሀገራት ወጣቶች ልምድ እንዲለዋወጡ የሚያስችሉ የመግባቢያ ሰነዶች ተፈርመዋል። የወቅቱ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦአከይ እ.አ.አ 2023 ፕሬዝዳንት ሆነው በተመረጡበት ወቅት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ለማደስ እና በንግድ ዘርፍ በጋራ ለመስራት ፍላጎታቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም ከተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ከላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦአካይ ጋር ውይይት አድርገዋል። የሁለትዮሽ ውይይቱ በቴክኖሎጂ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ኢትዮጵያ ለመገንባት ባቀደችው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ላይ ያተኮረ ነበር። በውይይቶቹ ላይ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በንግድ እና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። የላይቤሪያው ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ለስራ ጉብኝት ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክትም የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የነገ ብሩህ ተስፋ እየተሰራባት ወደ ምትገኘው ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ እንኳን በሰላም መጡ ብለዋል። በፕሬዝዳንቱ ቆይታ እጅግ ፍሬያማ ውይይት እንደሚኖራቸውም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። የፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የስራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ወዳጅነት የበለጠ እንደሚያጠናክርም ታምኖበታል። የኢትዮጵያ እና የላይቤሪያ መጻኢ ግንኙነት ከታሪካዊ ወዳጅነት ወደ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ አጋርነት የማሳደግ ፍላጎት በሁለቱም ወገን በኩል አለ። በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የአቪዬሽን ትስስር፣ የቴክኖሎጂ ልውውጥ እና በአህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጠና (AfCFTA) ማዕቀፍ የሚደረግ ትብብር ለጋራ ብልጽግና መሰረት ይጥላል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3912
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2666
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8455
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6944
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60900
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54902
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35399
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33015
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27998
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27270
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26762
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26313
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60900
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54902
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35399
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33015
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 529
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ
Apr 12, 2026 1012
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ በቀበኔሳ ገቢሳ ትንሣኤ ለሰው ልጅ ተስፋን፣ ዘለዓለማዊ ሕይወትን እና ከኃጢአት ነፃ መውጣትን የሚያበስር ኃይማኖታዊ በዓል ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ በመነሳቱ የሰው ልጅ የዘለዓለም የሕይወት አክሊልን ተስፋ ያደረገበት፣ የእግዚአብሔር ፍቅር የተገለጠበት እንዲሁም የሰው ልጅ ከዘለዓለም ሞትና ከኃጢአት ባርነት ነፃ የወጣበት የድኅነት፣ የፍቅር፣ የጽናትና የተስፋ ብርሃን ብስራት ነው፡፡ የትንሣኤ በዓል ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የመነሳቱ ታላቅ ምሥጢር የሚታሰብበት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ የሰው ልጅ ከውርደት ወደ ክብር፣ ከኃጢያት ባርነት ወደ ድኅነት እንዲሁም ከጉስቁልና ወደ ብሩህ ተስፋ የተሸጋገረበት የድል አዋጅ ነው። በዕለቱም በሞት ላይ ሕይወት፣ በሐዘን ላይ ደስታ፣ በቂም ላይ ይቅርታ ተበስሮበታል። ከበዓላት ሁሉ የላቀ የነጻነት ተምሳሌት ነው ትንሣኤ። 👉የትንሣኤ ሕያው አስተምሮ በዕለት ተዕለት ሕይወት ትንሣኤ ሲከበር ከሥርዓተ አምልኮ ባለፈ፣ በዓሉ የሚሰጠውን ታላቅ አስተምሮ ማጤን ይገባል። ትንሣኤ በየቀኑ ካለንበት ድካምና ውድቀት በአዲስ መንፈስ የመነሳት አቅም ነው። በዓሉ የሚያስተምረንን የጽናት፣ የተስፋና የአብሮነት ዕሴት በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ መኖር ያስፈልጋል። ለዚህም የተቸገሩን መርዳት፣ የታመሙትን መጠየቅና የተጣሉትን ማስታረቅ የበዓሉን ትርጉም እውነተኛ ያደርገዋል። 👉የኢትዮጵያ ትንሣኤ፤ በፈተና የጸና ብርሃን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዓሉን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የዘንድሮውን የትንሣኤ በዓል የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በፈታኝ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ሆና እያለች ነው። መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችንም እሾህ የበዛበት ሊሆን ይችላል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ፣ በጨለማ ወጥመድ ሊያሥሩን የሚሞክሩ መሰናክሎች ቢበዙም፣ እምነታችን ግን ከሕማማት በኋላ ትንሣኤ እንደሚመጣ ነው" ብለዋል፡፡ "ኢትዮጵያ ዛሬም ትንሳኤዋን እያየች ነው። መቃብሯ ተከፍቷል፤ ማኅተሙም ተሰብሯል። የትንሣኤውን ዜና ሊያደበዝዙ የሚሞክሩ የውሸት ወሬዎችና ተስፋ አስቆራጭ ትረካዎች የሀገራችንን የብርሃን ጉዞ ሊገቱት አይችሉም። ትንሳኤው እውነት ነው፤ ብርሃኑም የማይቀለበስ ሀቅ ሆኗል" ሲሉም አረጋግጠዋል፡፡ 👉ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ ምክክር፤ የተስፋ ምዕራፎች የኢትዮጵያ ትንሣኤ አንዱ መገለጫ ዴሞክራሲን የመገንባት ጽናት ነው። ትንሣኤ ያለ ሕማማት እንደማይገኝ ሁሉ ዴሞክራሲ ያለ ፈተና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ዴሞክራሲ የሚገነባው በጽናት እንጂ በፍርሃት አይደለም። ዴሞክራሲን እየገነባን በትዕግሥትና በቆራጥነት ወደ ተስፋዋ ምድር እንደርሳለን። አሁን ያለው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጦርነት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና ማህበራዊ አለመረጋጋት የትንሳኤን ትምህርት ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊ ያደርገዋል፡፡ ችግሮችን በብቸኝነት የምንወጣበት ጊዜ አብቅቷል። ዛሬ እንደህዝብ የሚያስፈልገን ከ"እኔ" ወደ "እኛ" መሸጋገር፣ የግል ፍላጎትን ለጋራ ስኬት መስዋዕት ማድረግ ግድ የሚልበት ወቅት ላይ ነን። የአንድነት ጉዟችንን በማጠናከር ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ጫናዎችን ለመቋቋም በጋራ መቆም ይገባናል። የተቸገሩትን በመርዳት፣ የታመሙትን በመጠየቅና የተጣሉትን በማስታረቅ የተግባር አብሮነትን በማሳየት የበዓሉን እውነተኛ ትርጉም መግለጥ ይገባል፡፡ 👉ምርጫ፤ ከኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበትና ተስፋ የታደሰበት ዕለት ነው። እኛም በምርጫ ካርዳችን የሃሳብ ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ አንድነት ድል በማድረግ የኢትዮጵያን የብልፅግና ትንሳኤ እናረጋግጣለን። በትንሣኤ በዓል የምንማረው ይቅርታና ጽናትም ለምርጫችን ስኬት አቅም ይሆናል። በኅብረት የምንሰጠው ድምፅም የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የመቅረጽ ኃይል በእጃችን መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው "ምርጫ የኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ነው። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም። በዓለም ላይ በደልዳላ መንገድ ተጉዞ ዴሞክራሲን የገነባ ሀገር የለም። ዴሞክራሲና ብልፅግና ያለ ጽናት አይሳኩም። ከእኛ በፊት ዐመጻውን በትዕግሥት የመከቱ ተሻግረዋል፤ ሑካታውን በጽናት ያለፉ አሳክተዋል። ብንመኝም ፈተናውን አናስቀርም፤ መጽናት ግን እንችላለን። ከድኅነት መውጫው ብርታታችን፣ ወደ ዴሞክራሲ መድረሻችው ትዕግሥታችን እንደሆነ አምነን ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በሙሉ ልባችን እንትጋ!!" ብለዋል። 👉የወደፊት እጣ ፈንታችን በእጃችን ከፊታችን የሚጠብቁን ሀገራዊ ምክክርና የ2018 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የወደፊት መጻኢ ዕድል የሚወስኑ ታላላቅ ሁነቶች ናቸው። እነዚህ ሂደቶች ስኬታማ የሚሆኑት እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን ሲወጣ ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በልባችን ውስጥ ይቅርታና አብሮነት ሲነግስ ብቻ ግቡን ይመታል። ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበት እንደሆነው ሁሉ፣ በምክክሩም ጥልን፣ ጥርጣሬን፣ ያለመግባባት መንፈስን ድል መንሳት ይገባል፤ ቅንነት፣ ተስፋና መተሳሰብ ለምክክሩ ስኬት የመተማመኛ ቁልፎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ 2018 ዓ.ም ደግሞ የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ ማሳያ አንጓ ነው፤ የዜጎች ነፃ ተሳትፎ መብታቸውን የሚያስከብሩበት ፍላጎታቸውን የሚያረጋግጡበት ማረጋገጫ ማህተም ጭምር፡፡ ዜጎች የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን የሚያስከብሩበት፤ የሌላውን ሃሳብ አክብረው የራሳቸውን የሚያስከብሩበት ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በጋራ የሚቆሙበት መድረክ ነው፡፡ ትንሣኤ የድልና የነጻነት በዓል ነው። ይህንን ታላቅ ዕለት ስናከብር ያለፈውን ቁስል ሽረን፣ ለነገ ተስፋ ሰንቀን መሆን አለበት። እርስ በእርስ በመደጋገፍ፣ ችግሮችን በንግግር በመፍታት ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ስኬታማነት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል። የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ እንቁም! መልካም የትንሳኤ በዓል!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም