ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር የዲጂታል ግብር ክፍያ ሥርዓት ጀመረ
Sep 12, 2026 69
ሰመራ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦የአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር የዲጂታል ግብር ክፍያ ሥርዓት ጀመረ። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሰመራ ሎጊያ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር አህመድ ኑርሳሊም፤ የዲጂታል የግብር ክፍያ ሥርዓት ቀልጣፋ አሰራርን ከመዘርጋት ባለፈ ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሚያስችል ዘመናዊ አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።   የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ለብልሹ አሰራር እንዳይጋለጥ እና የግብር መሰወር ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ግብር ከፋዮች ምንም አይነት እንግልት ሳይገጥማቸው ባሉበት ሆነው የሚከፍሉበት ስርአት መዘርጋቱ አስደሳች መሆኑን ተናግረዋል። ግብር ከፋዮች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና በቴሌብር አማራጮች ባሉበት ሆነው ግብራቸውን በመክፈል ከእንግልት በጸዳ መልኩ ሃላፊነታቸውን በቀላሉ መወጣት ያስችላቸዋል ብለዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኀላፊ ኡመር ኑር እና ሌሎችም የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ
Sep 12, 2026 81
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ):- በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የመጀመሪያ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሱዳኑን ሂላል አል-ሳሂልን 2 ለ 1 አሸንፏል። በድሬዳዋ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ካርሎስ ዳምጠው በ50ኛው እና በ56ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥሯል። ኢንሳ ሰኢድ ለሂላል አል-ሳሂል ጎሉን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሁለቱ ቡድኖች በድምር ውጤት ሶስት አቻ መሆናቸውን ተከትሎ ጨዋታው ወደ መለያ ምት አምርቷል። በዚህም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በመለያ ምት 4 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ሁለተኛ ዙር ማጣሪያ አልፏል። ወልዋሎ በሁለተኛው ዙር ከዛንዚባሩ ኬኤምኬኤም እና ከሊቢያው አል አህሊ ትሪፖሊ አሸናፊ ጋር ይጫወታል። አል አህሊ ትሪፖሊ በመጀመሪያው ጨዋታ 3 ለ 0 ያሸነፈ ሲሆን የመልሱ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ ይደረጋል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአህጉራዊ መድረክ ሲሳተፍ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የውድድሩ ተሳትፎውን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉን ተከትሎ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያዩ
Sep 12, 2026 92
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተው በኢትዮጵያ እና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ‎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‎ውይይታችን በመከላከያ እና ደኅንነት፣ በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት እንዲሁም በቴክኖሎጂ መስኮች ያለንን ትብብር ለማሳደግ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል።   እንዲሁም የትምህርት ልምድ ልውውጦችን ማስፋት፣ በባህል እና በሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መክረናል ነው ያሉት። ‎ ‎በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረገው ዝግጅት ያለን አጋርነት ጨምሮ ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብሮችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ መወያየታቸውንም አስታውቀዋል። በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረቱ የንግድ እና የኢኮኖሚ ልውውጦችን ይበልጥ ለማስፋፋትም በጋራ ለመሥራት መስማማታቸውን አረጋግጠዋል።
በትምህርት መሰረተ ልማት ላይ እየተከናወነ ያለው ልማት በትምህርት ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው
Sep 12, 2026 86
ነገሌ ቦረና ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን በትምህርት መሰረተ ልማት ላይ እየተከናወነ ያለው ልማት በጥራትና ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን የዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡ በዞኑ ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የተማሪ ክፍል ጥምርታን ለማመጣጠን 18 ቅድመ መደበኛ እና አምስት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸው ታውቋል። በኦሮሚያ ክልል የምስራቅ ቦረና ዞን የትምህርት ጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ዲዳ ገልገሎ፤ በአዲሱ ዓመት ለትምህርት የተደረገውን ዝግጅት በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።   በማብራሪያቸውም ለትምህርት ሴክተሩና አጠቃላይ ለመማር ማስተማሩ ሂደት በተለይም ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የተቀናጀ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። በመሆኑም በአዲሱ የትምህርት ዘመን ከ189 ሺህ 340 በላይ መደበኛ ተማሪዎችን ለመቀበል የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የተማሪ ክፍል ጥምርታን ለማመጣጠን 18 ቅድመ መደበኛ እና አምስት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። የትምህርት ቤቶቹ መገንባት በ2019 የትምህርት ዘመን ከ1 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎችን ለመቀበል የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል። በድምሩ ምስራቅ ቦረና ዞን በትምህርት መሰረተ ልማት ላይ እየተከናወነ ያለው ልማት በጥራትና ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። የነገሌ ቦረና ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ኑራ አብዱባ፤ በመንግስት ለትምህርት ሴክተሩ የተሰጠው ትኩረት ልጆቻችን የተሻለ የትምህርት እድል እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው ሲሉ ተናግረዋል።   አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን ከመገንባት በተጨማሪ የቆዩ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል በተደረገው የልማት ስራ የሁላችንም ተሳትፎ ተጨምሮበት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ አስደስቶናል ብለዋል። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ መቶ አለቃ አማረ አስራት፤ የትምህርት ቤት ግንባታ የትውልድ ግንባታ መሰረት በመሆኑ የሁላችንም ተሳትፎ የግድ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በህዝቡና በመንግስት ጠንካራ ትብብርም በዞኑ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻልና አዲስ በመገንባት ለመማር ማስተማሩ ዝግጁ እንዲሆኑ ተደርጓል ብለዋል። የትምህርት ተደራሽነትን ከማስፋት በተጨማሪ ለግብአት የሚሆኑ ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ በንቃት መሳተፋቸውን አንስተው ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል።
የሚታይ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያዩ
Sep 12, 2026 92
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተው በኢትዮጵያ እና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ‎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‎ውይይታችን በመከላከያ እና ደኅንነት፣ በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት እንዲሁም በቴክኖሎጂ መስኮች ያለንን ትብብር ለማሳደግ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል።   እንዲሁም የትምህርት ልምድ ልውውጦችን ማስፋት፣ በባህል እና በሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መክረናል ነው ያሉት። ‎ ‎በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረገው ዝግጅት ያለን አጋርነት ጨምሮ ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብሮችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ መወያየታቸውንም አስታውቀዋል። በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረቱ የንግድ እና የኢኮኖሚ ልውውጦችን ይበልጥ ለማስፋፋትም በጋራ ለመሥራት መስማማታቸውን አረጋግጠዋል።
‎‎በብሪክስ አባል ሀገራት ዘንድ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ እና ሰፊ ገበያ አለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 12, 2026 106
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦‎‎በብሪክስ አባል ሀገራት ዘንድ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ እና ሰፊ ገበያ አለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት በሚል መሪ ቃል በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ አካል በመሆናችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል።   ‎‎በብሪክስ አባል ሀገራት ዘንድ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ እና ሰፊ ገበያ አለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁን ያለው መልካም ዕድል እነዚህን አቅሞች በማስተሳሰር የላቀ እሴት መፍጠር እና ይህ እሴት ደግሞ ሀብቱ በሚገኝበት ቦታ መመረት እንዲችል ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በማዕድን ልማት፣ በታዳሽ ኃይል እና እያደገ በሚገኘው የኢንዱስትሪ መሠረቷ ላይ እነዚህን አጋርነቶች ለመገንባት ዝግጁ ናትም ብለዋል።   ‎‎በተጨማሪም በአሠራር ሥርዓቶቻችን ውስጥ ጽናትን መገንባት፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የአህጉራችንን ፍላጎት እንዲያገለግል ማድረግ፣ አስተማማኝ የዕዳ እፎይታ ሒደትን ማሳደግ እንዲሁም የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራዎችን ከኢኮኖሚ ሽግግር ጋር ማስተሳሰር ይኖርብናል ሲሉም ገልጸዋል። ‎‎የብሪክስ መድረክ የጋራ ትብብርን ወደ የጋራ እሴት፣ ጽናት እና ዘላቂ ዕድገት የመለወጥ ሰፊ አቅምና ቁርጠኝነት እንዳለውም ነው ያመላከቱት።
በትምህርት ዘርፍ የተወሰዱ ውጤታማ የማሻሻያ እርምጃዎች በትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ ነው
Sep 12, 2026 245
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦በትምህርት ዘርፍ የተወሰዱ ውጤታማ የማሻሻያ እርምጃዎች በትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። የትምህርት ሚኒስትሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ መንግሥት የተሟላ ዜጋ የማፍራት፣ የግብረገብና የእውቀት መለኪያዎችን የማጠናከር እንዲሁም የመንግሥትና የግል ትምህርት ቤቶችን የጥራት ልዩነት በማጥበብ የትምህርት አሰጣጡን ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገር ሰፊ የሪፎርም ስራዎችን አከናውኗል። በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጥራት ያለውና በእውቀት የተካነ ትውልድ ለማፍራት የተከናወኑት ስራዎች ውጤት እያሳዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡   የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ታማኝነትን ለማረጋገጥ ሲባል የ12ኛ ክፍል ፈተናዎች በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ እንዲሰጡ መደረጉ የትምህርት አሰጣጡን እውነተኛ ገጽታ ማሳየት ማስቻሉን ጠቁመዋል። ከውጤት መሻሻል አንጻር በተደረጉ የማሻሻያ ተግባራትና በትምህርት ጥራት ቁጥጥር በ2018 የትምህርት ዘመን ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች ምጣኔ ወደ 12 ነጥብ 8 በመቶ ከፍ ማለቱን አስረድተዋል። ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ተማሪዎች በልዩ ድጋፍና ክትትል በማስተማር ለሀገር ዕድገት የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የትምህርት ሚኒስቴር ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ በ2018 የትምህርት ዘመን በቦንጋ፣ በጅግጅጋ፣ በጋምቤላ፣ በወሊሶና ቡኢ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡ ይህንን ውጤታማ አሰራር ለማስፋት በያዘው ዕቅድ መሰረት በ2019 የትምህርት ዘመን የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ቁጥር ወደ ዘጠኝ ለማሳደግ በአርባ ምንጭ፣ በባህርዳር፣ በድሬዳዋ እና በአሶሳ ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ 13 አዳዲስ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመገንባት ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል።   ከትምህርት ግብዓትና ቴክኖሎጂ አንጻርም የኮምፒውተር ላቦራቶሪዎችን በማስፋፋት፣ የዲጂታል መጽሐፍትንና የኢንተርኔት መሠረተ ልማቶችን ወደ ትምህርት ቤቶች በመዘርጋት የተማሪዎችን የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት የማሳደግ ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል፡፡ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ማህበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ 146 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ሀብት በገንዘብና በዓይነት ማሰባሰብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ሀብት 14 ሺህ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ለተማሪዎች ምቹ ሆነው መታደሳቸውን ጠቁመዋል፡፡ በሌላ በኩል የተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ የማቋረጥ መጠንን ለመቀነስና የመማር ብቃታቸውን ለማሳደግ በተዘረጋው የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም በሀገር አቀፍ ደረጃ ወደ 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚጠጉ ተማሪዎች የምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ወደ ራስ ገዝነት ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፤ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ምደባም በውድድር፣ በእውቀትና በችሎታ ላይ ብቻ በተመሰረተ ግልጽ አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል። ከተከናወኑት የሥርዓተ-ትምህርት ክለሳዎች፣ የግብረገብና የታሪክ ትምህርቶች መካተት እንዲሁም ከመዋቅራዊ ሪፎርሞች አንጻር ሀገሪቱን በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢኮኖሚና በፖለቲካ ዘርፎች በብቃት ሊመሩ የሚችሉ ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ማፍራት የሚያስችል ትክክለኛ መሠረት ተጥሏል ብለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያዩ
Sep 12, 2026 92
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተው በኢትዮጵያ እና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ‎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‎ውይይታችን በመከላከያ እና ደኅንነት፣ በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት እንዲሁም በቴክኖሎጂ መስኮች ያለንን ትብብር ለማሳደግ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል።   እንዲሁም የትምህርት ልምድ ልውውጦችን ማስፋት፣ በባህል እና በሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መክረናል ነው ያሉት። ‎ ‎በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረገው ዝግጅት ያለን አጋርነት ጨምሮ ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብሮችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ መወያየታቸውንም አስታውቀዋል። በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረቱ የንግድ እና የኢኮኖሚ ልውውጦችን ይበልጥ ለማስፋፋትም በጋራ ለመሥራት መስማማታቸውን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያና ሕንድ ግንኙነት ወደ አዲስ የታሪካዊ ትብብር ከፍታ ይሸጋገራል -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 12, 2026 207
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ሕንድ ግንኙነት ወደ አዲስ የታሪካዊ ትብብር ከፍታ ይሸጋገራል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለቱን ሀገራት አጋርነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል። በውይይታቸውም የመከላከያ ትብብርን ማሳደግ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የአቅም ግንባታ፣ የማዕድን ዘርፍ እንዲሁም ወደ COP32 በሚደረገው ጉዞ ላይ ትኩረት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።   እነዚህ የትብብር መስኮች የተግባር ትብብርን ለማጠናከር እና ለሁለቱ ሀገራት ሕዝቦች አዳዲስ እድሎችን ለመፍጠር ከፍተኛ አቅም እንዳላቸውም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እና ሕንድ ጥልቅ ታሪካዊ ግንኙነት፣ የቆየ የባህል ትስስር እና በሕዝቦቻቸው መካከል ጠንካራ ወዳጅነት ያላቸው ቢሆንም፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ብዙ አቅም አሁንም ጥቅም ላይ ሳይውል የቀረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በመሆኑም የታሪክ እና የመልካም ፈቃድ ትስስሩን በቴክኖሎጂ፣ በክህሎት፣ በኢንቨስትመንት፣ በዘላቂ ልማት እና በተጠናከረ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ ወደተመሠረተ የበለጠ ታላቅና የጋራ ተጠቃሚነትን ወደሚያረጋግጥ አጋርነት ለመቀየር ትክክለኛው ጊዜ አሁን ነው ብለዋል።
አዲሱ አመት የመከላከያ ሠራዊታችን አቅም ይበልጥ የሚጠናከርበት ዓመት ይሆናል - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Sep 11, 2026 516
አዲስ አበባ ፤ጳጉሜን 5 /2018 (ኢዜአ)፦አዲሱ ዓመት የመከላከያ ሠራዊታችን አቅም ይበልጥ የሚጠናከርበትና ዝግጁነቱ የሚያድግበት ዓመት ይሆናል ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ፡፡ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና ለመከላከያ ሠራዊት አባላት ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ባስተላለፉት መልዕክት፤ 2018 በርካታ ፈተናዎች የተጋፈጥንበት ዓመት ቢሆንም፣ የመከላከያ ሠራዊቱ የተቀመጡ ሀገራዊ ግቦችንና ዕቅዶችን በተቀናጀ አሠራር በማሳካት የተሰጠውን ኃላፊነት በከፍተኛ ብቃት የተወጣበት ዓመት ነበር ብለዋል። በተጠናቀቀው ዓመት የሠራዊቱ ዋና ትኩረት የሀገርን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ፣ ህዝብን መጠበቅና የልማት ጉዞዎችን ከዕንቅፋት መከላከል እንደነበር ጠቁመው፤ በዚህም በተለያዩ አካባቢዎች መረጋጋት በመፍጠር ህዝቡ ወደ መደበኛ ኑሮው እንዲመለስ መደረጉን አስረድተዋል። አክለውም ዘላቂ ሰላም በወታደራዊ አቅም ብቻ የማይረጋገጥ በመሆኑ ህዝቡ ለሰላም የሚያበረክተውን ሚና ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። በሌላ በኩል 2018 ዓ.ም የመከላከያ አቅምን ከዘመኑ ጋር ለማዛመድ ከአናሎግ ወደ ዲጂታል አሠራር የመሸጋገር፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የመታጠቅ፣ የምድርና የአየር ኃይል አቅምን የማሳደግ እንዲሁም የመከላከያ ኢንዱስትሪን በሀገር ውስጥ ምርቶች የማጠናከር ሰፊ ሥራ የተሠራበት ዓመት መሆኑን ገልፀዋል። በመጪው 2019 ዓ.ም የመከላከያ ሠራዊቱ ሁለት ዋና ዋና ትኩረቶች ይኖሩታል ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ የመጀመሪያው የሀገርን ሰላም፣ ደህንነትና ሉዓላዊነት ማስጠበቅ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የሠራዊቱን የማድረግ አቅም፣ የሰው ኃይል፣ የሥልጠና፣ የመሠረተ ልማት እና የመከላከያ ኢንዱስትሪ ልማት ሥራዎችን ወደተሻለ ደረጃ ማሸጋገር እንደሆነ አስታውቀዋል። አዲሱ ዓመት የመከላከያ ሠራዊታችን አቅም ይበልጥ የሚጠናከርበትና ዝግጁነቱ የሚያድግበት ዓመት ይሆናል ሲሉም አክለዋል፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ለጀግናው የመከላከያ ሠራዊት አመራሮች፣ መኮንኖች፣ ወታደሮችና ሲቪል ሠራተኞች መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆን ተመኝተው፤ አዲሱ ዘመን ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ ለህዝባችን ደህንነትና ብልፅግና፣ ለሰራዊታችን የበለጠ አቅም፣ ዝግጁነትና ስኬት የሚያመጣ ዓመት ይሁንልን ሲሉም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
ፖለቲካ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያዩ
Sep 12, 2026 92
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተው በኢትዮጵያ እና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ‎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‎ውይይታችን በመከላከያ እና ደኅንነት፣ በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት እንዲሁም በቴክኖሎጂ መስኮች ያለንን ትብብር ለማሳደግ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል።   እንዲሁም የትምህርት ልምድ ልውውጦችን ማስፋት፣ በባህል እና በሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መክረናል ነው ያሉት። ‎ ‎በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረገው ዝግጅት ያለን አጋርነት ጨምሮ ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብሮችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ መወያየታቸውንም አስታውቀዋል። በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረቱ የንግድ እና የኢኮኖሚ ልውውጦችን ይበልጥ ለማስፋፋትም በጋራ ለመሥራት መስማማታቸውን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያና ሕንድ ግንኙነት ወደ አዲስ የታሪካዊ ትብብር ከፍታ ይሸጋገራል -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 12, 2026 207
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ሕንድ ግንኙነት ወደ አዲስ የታሪካዊ ትብብር ከፍታ ይሸጋገራል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለቱን ሀገራት አጋርነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል። በውይይታቸውም የመከላከያ ትብብርን ማሳደግ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የአቅም ግንባታ፣ የማዕድን ዘርፍ እንዲሁም ወደ COP32 በሚደረገው ጉዞ ላይ ትኩረት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።   እነዚህ የትብብር መስኮች የተግባር ትብብርን ለማጠናከር እና ለሁለቱ ሀገራት ሕዝቦች አዳዲስ እድሎችን ለመፍጠር ከፍተኛ አቅም እንዳላቸውም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እና ሕንድ ጥልቅ ታሪካዊ ግንኙነት፣ የቆየ የባህል ትስስር እና በሕዝቦቻቸው መካከል ጠንካራ ወዳጅነት ያላቸው ቢሆንም፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ብዙ አቅም አሁንም ጥቅም ላይ ሳይውል የቀረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በመሆኑም የታሪክ እና የመልካም ፈቃድ ትስስሩን በቴክኖሎጂ፣ በክህሎት፣ በኢንቨስትመንት፣ በዘላቂ ልማት እና በተጠናከረ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ ወደተመሠረተ የበለጠ ታላቅና የጋራ ተጠቃሚነትን ወደሚያረጋግጥ አጋርነት ለመቀየር ትክክለኛው ጊዜ አሁን ነው ብለዋል።
አዲሱ አመት የመከላከያ ሠራዊታችን አቅም ይበልጥ የሚጠናከርበት ዓመት ይሆናል - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Sep 11, 2026 516
አዲስ አበባ ፤ጳጉሜን 5 /2018 (ኢዜአ)፦አዲሱ ዓመት የመከላከያ ሠራዊታችን አቅም ይበልጥ የሚጠናከርበትና ዝግጁነቱ የሚያድግበት ዓመት ይሆናል ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ፡፡ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና ለመከላከያ ሠራዊት አባላት ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ባስተላለፉት መልዕክት፤ 2018 በርካታ ፈተናዎች የተጋፈጥንበት ዓመት ቢሆንም፣ የመከላከያ ሠራዊቱ የተቀመጡ ሀገራዊ ግቦችንና ዕቅዶችን በተቀናጀ አሠራር በማሳካት የተሰጠውን ኃላፊነት በከፍተኛ ብቃት የተወጣበት ዓመት ነበር ብለዋል። በተጠናቀቀው ዓመት የሠራዊቱ ዋና ትኩረት የሀገርን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ፣ ህዝብን መጠበቅና የልማት ጉዞዎችን ከዕንቅፋት መከላከል እንደነበር ጠቁመው፤ በዚህም በተለያዩ አካባቢዎች መረጋጋት በመፍጠር ህዝቡ ወደ መደበኛ ኑሮው እንዲመለስ መደረጉን አስረድተዋል። አክለውም ዘላቂ ሰላም በወታደራዊ አቅም ብቻ የማይረጋገጥ በመሆኑ ህዝቡ ለሰላም የሚያበረክተውን ሚና ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። በሌላ በኩል 2018 ዓ.ም የመከላከያ አቅምን ከዘመኑ ጋር ለማዛመድ ከአናሎግ ወደ ዲጂታል አሠራር የመሸጋገር፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የመታጠቅ፣ የምድርና የአየር ኃይል አቅምን የማሳደግ እንዲሁም የመከላከያ ኢንዱስትሪን በሀገር ውስጥ ምርቶች የማጠናከር ሰፊ ሥራ የተሠራበት ዓመት መሆኑን ገልፀዋል። በመጪው 2019 ዓ.ም የመከላከያ ሠራዊቱ ሁለት ዋና ዋና ትኩረቶች ይኖሩታል ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ የመጀመሪያው የሀገርን ሰላም፣ ደህንነትና ሉዓላዊነት ማስጠበቅ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የሠራዊቱን የማድረግ አቅም፣ የሰው ኃይል፣ የሥልጠና፣ የመሠረተ ልማት እና የመከላከያ ኢንዱስትሪ ልማት ሥራዎችን ወደተሻለ ደረጃ ማሸጋገር እንደሆነ አስታውቀዋል። አዲሱ ዓመት የመከላከያ ሠራዊታችን አቅም ይበልጥ የሚጠናከርበትና ዝግጁነቱ የሚያድግበት ዓመት ይሆናል ሲሉም አክለዋል፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ለጀግናው የመከላከያ ሠራዊት አመራሮች፣ መኮንኖች፣ ወታደሮችና ሲቪል ሠራተኞች መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆን ተመኝተው፤ አዲሱ ዘመን ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ ለህዝባችን ደህንነትና ብልፅግና፣ ለሰራዊታችን የበለጠ አቅም፣ ዝግጁነትና ስኬት የሚያመጣ ዓመት ይሁንልን ሲሉም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
ማህበራዊ
በትምህርት መሰረተ ልማት ላይ እየተከናወነ ያለው ልማት በትምህርት ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው
Sep 12, 2026 86
ነገሌ ቦረና ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን በትምህርት መሰረተ ልማት ላይ እየተከናወነ ያለው ልማት በጥራትና ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን የዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡ በዞኑ ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የተማሪ ክፍል ጥምርታን ለማመጣጠን 18 ቅድመ መደበኛ እና አምስት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸው ታውቋል። በኦሮሚያ ክልል የምስራቅ ቦረና ዞን የትምህርት ጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ዲዳ ገልገሎ፤ በአዲሱ ዓመት ለትምህርት የተደረገውን ዝግጅት በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።   በማብራሪያቸውም ለትምህርት ሴክተሩና አጠቃላይ ለመማር ማስተማሩ ሂደት በተለይም ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የተቀናጀ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። በመሆኑም በአዲሱ የትምህርት ዘመን ከ189 ሺህ 340 በላይ መደበኛ ተማሪዎችን ለመቀበል የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የተማሪ ክፍል ጥምርታን ለማመጣጠን 18 ቅድመ መደበኛ እና አምስት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። የትምህርት ቤቶቹ መገንባት በ2019 የትምህርት ዘመን ከ1 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎችን ለመቀበል የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል። በድምሩ ምስራቅ ቦረና ዞን በትምህርት መሰረተ ልማት ላይ እየተከናወነ ያለው ልማት በጥራትና ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። የነገሌ ቦረና ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ኑራ አብዱባ፤ በመንግስት ለትምህርት ሴክተሩ የተሰጠው ትኩረት ልጆቻችን የተሻለ የትምህርት እድል እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው ሲሉ ተናግረዋል።   አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን ከመገንባት በተጨማሪ የቆዩ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል በተደረገው የልማት ስራ የሁላችንም ተሳትፎ ተጨምሮበት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ አስደስቶናል ብለዋል። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ መቶ አለቃ አማረ አስራት፤ የትምህርት ቤት ግንባታ የትውልድ ግንባታ መሰረት በመሆኑ የሁላችንም ተሳትፎ የግድ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በህዝቡና በመንግስት ጠንካራ ትብብርም በዞኑ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻልና አዲስ በመገንባት ለመማር ማስተማሩ ዝግጁ እንዲሆኑ ተደርጓል ብለዋል። የትምህርት ተደራሽነትን ከማስፋት በተጨማሪ ለግብአት የሚሆኑ ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ በንቃት መሳተፋቸውን አንስተው ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል።
በትምህርት ዘርፍ የተወሰዱ ውጤታማ የማሻሻያ እርምጃዎች በትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ ነው
Sep 12, 2026 245
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦በትምህርት ዘርፍ የተወሰዱ ውጤታማ የማሻሻያ እርምጃዎች በትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። የትምህርት ሚኒስትሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ መንግሥት የተሟላ ዜጋ የማፍራት፣ የግብረገብና የእውቀት መለኪያዎችን የማጠናከር እንዲሁም የመንግሥትና የግል ትምህርት ቤቶችን የጥራት ልዩነት በማጥበብ የትምህርት አሰጣጡን ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገር ሰፊ የሪፎርም ስራዎችን አከናውኗል። በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጥራት ያለውና በእውቀት የተካነ ትውልድ ለማፍራት የተከናወኑት ስራዎች ውጤት እያሳዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡   የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ታማኝነትን ለማረጋገጥ ሲባል የ12ኛ ክፍል ፈተናዎች በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ እንዲሰጡ መደረጉ የትምህርት አሰጣጡን እውነተኛ ገጽታ ማሳየት ማስቻሉን ጠቁመዋል። ከውጤት መሻሻል አንጻር በተደረጉ የማሻሻያ ተግባራትና በትምህርት ጥራት ቁጥጥር በ2018 የትምህርት ዘመን ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች ምጣኔ ወደ 12 ነጥብ 8 በመቶ ከፍ ማለቱን አስረድተዋል። ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ተማሪዎች በልዩ ድጋፍና ክትትል በማስተማር ለሀገር ዕድገት የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የትምህርት ሚኒስቴር ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ በ2018 የትምህርት ዘመን በቦንጋ፣ በጅግጅጋ፣ በጋምቤላ፣ በወሊሶና ቡኢ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡ ይህንን ውጤታማ አሰራር ለማስፋት በያዘው ዕቅድ መሰረት በ2019 የትምህርት ዘመን የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ቁጥር ወደ ዘጠኝ ለማሳደግ በአርባ ምንጭ፣ በባህርዳር፣ በድሬዳዋ እና በአሶሳ ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ 13 አዳዲስ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመገንባት ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል።   ከትምህርት ግብዓትና ቴክኖሎጂ አንጻርም የኮምፒውተር ላቦራቶሪዎችን በማስፋፋት፣ የዲጂታል መጽሐፍትንና የኢንተርኔት መሠረተ ልማቶችን ወደ ትምህርት ቤቶች በመዘርጋት የተማሪዎችን የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት የማሳደግ ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል፡፡ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ማህበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ 146 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ሀብት በገንዘብና በዓይነት ማሰባሰብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ሀብት 14 ሺህ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ለተማሪዎች ምቹ ሆነው መታደሳቸውን ጠቁመዋል፡፡ በሌላ በኩል የተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ የማቋረጥ መጠንን ለመቀነስና የመማር ብቃታቸውን ለማሳደግ በተዘረጋው የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም በሀገር አቀፍ ደረጃ ወደ 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚጠጉ ተማሪዎች የምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ወደ ራስ ገዝነት ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፤ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ምደባም በውድድር፣ በእውቀትና በችሎታ ላይ ብቻ በተመሰረተ ግልጽ አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል። ከተከናወኑት የሥርዓተ-ትምህርት ክለሳዎች፣ የግብረገብና የታሪክ ትምህርቶች መካተት እንዲሁም ከመዋቅራዊ ሪፎርሞች አንጻር ሀገሪቱን በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢኮኖሚና በፖለቲካ ዘርፎች በብቃት ሊመሩ የሚችሉ ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ማፍራት የሚያስችል ትክክለኛ መሠረት ተጥሏል ብለዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከ2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ሆነዋል
Sep 12, 2026 112
ደሴ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ) ፦ በደቡብ ወሎ ዞን የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት እስካሁን ከ2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የዞኑ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የዜጎች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ንቅናቄና ተሳትፎ ቡድን መሪ ምስጋናው ደምሴ፤ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ በዞኑ በክረምቱ የተከናወኑ የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራትን ገልጸዋል።በዞኑ በክረምቱ ከ1ጥብ 2 ሚሊዮን በላይ በጎ ፈቃደኞች ነፃ አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል። በዚህም የቤት እድሳትና ግንባታ፣ የግብርና ስራዎችን የማገዝ፣ ለተማሪዎች የደብተርና ሌሎች ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ እንዲሁም የደም ልገሳና ሌሎችንም ማህበራዊ አገልግሎቶችን በማከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል።   በእስካሁኑ አገልግሎታቸው ከ2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው ይህም ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። ከአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች መካከል በዞኑ ቃሉ ወረዳ የሚኖሩት አርሶ አደር ደሳለኝ አህመድ፤ ከአንድ ሄክታር በላይ መሬታቸው በበጎ ፈቃደኞች ታርሶ በዘር የተሸፈላቸው መሆኑን ተናግረዋል።   የእርሻ ማሳቸውን በዘር ለመሸፈን አቅመ ደካማ በመሆናቸው ይቸገሩ እንደነበር አንስተው በተደረገላቸው ድጋፍና መልካም ተግባር ለሁሉም ምስጋና አቅርበዋል። በዞኑ ተሁለደሬ ወረዳ የሚኖሩት ወይዘሮ ሰዓዳ የሱፍ፤ የመኖሪያ ቤታቸው በእርጅና ምክንያት በተለይም በክረምት ለዝናብና ለብርድ ይዳርጋቸው እንደነበር አስታውሰው አዲስ ቤት ተሰርቶ የተሰጣቸው በመሆኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል። በአዲስ ዓመት በተሰራላቸው ቤት አዲስ ህይወት መኖር መጀመራቸውንም ገልጸው ለበጎ አድራጊዎች ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በክልሉ የወባ ወረርሽኝን ቀድሞ ለመከላከል የኬሚካል ርጭትና የአካባቢ ቁጥጥር ሥራ እየተከናወነ ነው
Sep 12, 2026 196
ባህር ዳር፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የክረምት መውጣትን ተከትሎ ሊከሰት የሚችል የወባ ወረርሽኝ ለመከላከል የኬሚካል ርጭትና የአካባቢ ቁጥጥር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የወባ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ዳምጤ ላንክር ለኢዜአ እንደገለጹት በዘንድሮ የክረምት ወቅት የተስተዋለው የዝናብ ሥርጭት መቆራረጥ ለወባ ትንኝ መራቢያ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ያደርጋል።   በመሆኑም ቢሮው በክልሉ የወባ በሽታ ስርጭት በስፋት ሊከሰትባቸው ይችላል ተብለው በተለዩ 17 ወረዳዎች ላይ የኬሚኬል ርጭት እያካሄደ መሆኑን ገልፀዋል። የኬሚካል ‎ርጭቱ ከነሀሴ ወር 2018 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ ቤት ለቤት እየተካሄደ ሲሆን ለዚህም 224 ሺህ 930 ኪሎ ግራም የፀረ ወባ ኬሚካል ጥቅም ላይ እየዋለ ይገኛል ብለዋል። በዚህም 471 ሺህ 578 መኖሪያ ቤቶች ላይ ርጭት እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት አቶ ዳምጤ፣ የኬሚካል ርጭት ሥራው 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚጠጉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ከወባ በሽታ ይታደጋል ብለዋል። እንደእሳቸው ገለጻ ‎ከኬሚካል ርጭቱ በተጨማሪ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማህበረሰቡን በማስተባበር ለወባ መራቢያ አመቺ የሆኑ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማፋሰስና የማዳፈን ሥራ ተከናውኗል። ‎ከተያዘው መስከረም ጀምሮ እስከ ታህሳስ ወር የወባ ትንኝ በስፋት የሚራባበት ወቅት መሆኑን አቶ ዳምጤ ገልጸው፣ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተጀመረው የኬሚካል ርጭትና የአካባቢ ቁጥጥር ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   በክልሉ "የአርብ ጠንካራ እጆች በሽታን ይገታሉ" በሚል መሪ ሀሳብ የተጀመረው የአካባቢ ቁጥጥር ሥራ በየሳምንቱ ይቀጥላል ብለዋል። ህብረተሰቡ ከአካባቢ ቁጥጥር ሥራው ጎን ለጎን የወባ በሽታ መከላከያ አልጋ አጎበርን በአግባቡ መጠቀም እንዳለበት ገልጸው፣ የወባ በሽታ ምልክት ሲያይም ወደጤና ተቋማት ፈጥኖ በመሄድ እንዲታከም አሳስበዋል። በደቡብ ጎንደር ዞን የፈገራ ወረዳ አርሶ አደር አለሙ ሙጬ በበኩላቸው እንዳሉት፣ የወባ በሽታን ቀድመው ለመከላከል በቤት ውስጥ የአልጋ አጎበር ከመጠቀም ባለፈ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማዳፈንና የማፋሰስ ሥራ እያከናወኑ ይገኛሉ። የክረምት ዝናብ መቆራረጥን ተከትሎ የወባ በሽታ እንዳይቀሰቀሰ የአካባቢ ቁጥጥር ስራን በየጊዜው እያከናወኑ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደር ዳኘ ዋለ ናቸው። ‎ቀደም ሲል የተሰጣቸውን የአልጋ አጎበር በአግባቡ በመጠቀም ቤተሰቦቻቸውን ከወባ በሽታ መታደግ እንደቻሉም ገልፀዋል።
ኢኮኖሚ
‎‎በብሪክስ አባል ሀገራት ዘንድ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ እና ሰፊ ገበያ አለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 12, 2026 106
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦‎‎በብሪክስ አባል ሀገራት ዘንድ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ እና ሰፊ ገበያ አለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት በሚል መሪ ቃል በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ አካል በመሆናችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል።   ‎‎በብሪክስ አባል ሀገራት ዘንድ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ እና ሰፊ ገበያ አለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁን ያለው መልካም ዕድል እነዚህን አቅሞች በማስተሳሰር የላቀ እሴት መፍጠር እና ይህ እሴት ደግሞ ሀብቱ በሚገኝበት ቦታ መመረት እንዲችል ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በማዕድን ልማት፣ በታዳሽ ኃይል እና እያደገ በሚገኘው የኢንዱስትሪ መሠረቷ ላይ እነዚህን አጋርነቶች ለመገንባት ዝግጁ ናትም ብለዋል።   ‎‎በተጨማሪም በአሠራር ሥርዓቶቻችን ውስጥ ጽናትን መገንባት፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የአህጉራችንን ፍላጎት እንዲያገለግል ማድረግ፣ አስተማማኝ የዕዳ እፎይታ ሒደትን ማሳደግ እንዲሁም የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራዎችን ከኢኮኖሚ ሽግግር ጋር ማስተሳሰር ይኖርብናል ሲሉም ገልጸዋል። ‎‎የብሪክስ መድረክ የጋራ ትብብርን ወደ የጋራ እሴት፣ ጽናት እና ዘላቂ ዕድገት የመለወጥ ሰፊ አቅምና ቁርጠኝነት እንዳለውም ነው ያመላከቱት።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የተቀረጹት ዘርፎች ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው 
Sep 12, 2026 121
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የተቀረጹት ዋና ዋና ዘርፎችና ሌሎችም ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ዘመዴነህ ንጋቱ ገለጹ፡፡ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ባወጣው የቅርብ ጊዜ መረጃ መሰረት፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ከተመዘገበባቸው ጥቂት ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን አንስተዋል፡፡ ይህም በሀገሪቱ ከተተገበሩት መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና ከተከተለችው የረጅም ጊዜ የልማት ስትራቴጂ የሚመነጭ መሆኑን አመልክተዋል። በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያው በተተገበረባቸው ዘርፎች ማለትም በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በማዕድን እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች የተመዘገቡት ውጤቶች አበረታች ናቸው ብለዋል። በተለይም በማዕድን ዘርፍ በሀገሪቱ የታሪክ ሂደት ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ የወርቅ ኤክስፖርት ገቢ መመዝገቡን የጠቀሱት ባለሙያው፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ ከወርቅ የወጪ ንግድ 5 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ማግኘት መቻሉ የሪፎርሙ ትልቅ ስኬት መሆኑን አብራርተዋል። በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የ“ኢትዮጵያ ታመርት” ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ የሀገር ውስጥ ምርት አቅምን በማሳደግና የማምረት ሂደትን በማጠናከር ረገድ ከነበረበት መነሻ ተነስቶ ከፍተኛ ዕድገት ማሳየቱን ጠቅሰዋል። በግብርናው ዘርፍ ከተለመደው ባህላዊ አሰራር ወደ ዘመናዊና ሜካናይዝድ አሰራር በመሸጋገር ቀደም ሲል በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ ይገቡ የነበሩ ምርቶችን ማስቀረት የተቻለ ሲሆን፣ ምርቶቹን ለውጭ ገበያ ማቅረብ የተጀመረበት አዲስ ምዕራፍ መከፈቱን ተናግረዋል፡፡ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂው ዘርፍ፣ በተለይም ለአርቲፊሻል ኢንቴሊጀንስ (AI) የሰጠችው ከፍተኛ ትኩረትና የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራቷ በኦፊሴላዊ መልኩ በአፍሪካ ደረጃ ተወዳዳሪና መሪ የሚያደርጋት ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው ብለዋል። በቱሪዝም ዘርፉ የገበታ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ በኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች የተከናወኑት የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎችና የመዳረሻ ልማት ሥራዎች የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ለኢኮኖሚ ዕድገት እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም በአገልግሎት ዘርፍ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ በትርፋማነቱ፣ በኔትወርክ ማስፋፋቱና በስኬታማነት መቀጠሉን ጠቅሰዋል፡፡ በፋይናንስ ዘርፉም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ጨምሮ ሌሎች የግል ባንኮች ያስመዘገቡት በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የትርፍ መጠን በሀገሪቱ የጎላ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መኖሩን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። ሀገሪቱ ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላትን መሰረት በማጠናከር ረገድ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ የመሰረተ ልማትና የጋዝ ፕሮጀክቶች መጀመራቸውና መጠናቀቃቸው ለኢኮኖሚው ከፍተኛ እንቅስቃሴ መፍጠራቸውን ጠቁመዋል። ለአብነትም የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ከአምስት ሺህ ሜጋዋት ወደ 10 ሺህ ሜጋዋት ገደማ በእጥፍ ማሳደግ መቻሉን አሳታውቀዋል። የኢትዮጵያ የግል ባለሀብቶች ከሀገር ውስጥ አልፈው በውጭ ሀገራት ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የሀገር ውስጥ የግሉ ዘርፍ አቅሙን አጠናክሮ በመቀጠል በክልሉና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ጠንካራ የሚያደርጉ ግዙፍ ኩባንያዎችን መፍጠር እንደሚገባው አሳስበዋል።          
የኢትዮጵያና ብራዚል የኢኮኖሚ፣ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት ወደ አዲስና ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው
Sep 12, 2026 144
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ብራዚል የኢኮኖሚ፣ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት ወደ አዲስና ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን በኢትዮጵያ የብራዚል አምባሳደር ዣንዲር ፈሬራ ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ የብራዚል አምባሳደር ዣንዲር ፈሬራ ዶስ ሳንቶስ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያና ብራዚል መካከል የኢኮኖሚ፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የስትራቴጂካዊ ዘርፎች ያለው አጋርነት እየሰፋ መጥቷል። በዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት ወደ አዲስና ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ይገኛል ብለዋል። ብራዚል በአፍሪካ የመጀመሪያውን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ ኤጀንሲ (ApexBrasil) ጽሕፈት ቤት በአዲስ አበባ የከፈተች መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ የኢኮኖሚ፣ የንግድ እና የፖለቲካ ትብብር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል። የብራዚል ባለሀብቶች የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድሎች እና የግል ዘርፍ አቅም እንዲረዱ፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የጠበቀ የሁለትዮሽ ትብብር እንዲፈጥሩ ያመቻቻል ብለዋል። የግብርና ዘርፍ የሁለቱም ሀገራት ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በመሆኑ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶት ከሚሰሩባቸው ዋነኛ የትብብር መስኮች አንዱ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ብራዚል ኢትዮጵያ እየተገበረች ከምትገኘው የ"አረንጓዴ አሻራ" መርሃ-ግብር ትልቅ ተሞክሮ እንደምትወስድ ጠቁመዋል። ባለፉት አራት ዓመታት በአዲስ አበባ በነበራቸው ቆይታ በሀገሪቱ የተመዘገቡ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን፣ የሀገራዊ ምክክር ጉባዔን እና የመሠረተ ልማት ዕድገቶችን መታዘባቸውን ገልጸዋል።
‎‎ኢትዮጵያና ማሌዢያ ጠንካራ የኢኮኖሚ አጋርነት ለመመስረት የሚያስችል ከፍተኛ አቅም አላቸው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 12, 2026 122
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦‎‎ኢትዮጵያና ማሌዢያ ጠንካራ የኢኮኖሚ አጋርነት ለመመስረት የሚያስችል ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ‎‎ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ በሕዳር 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ካደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት የተገኘውን መልካም ዕድል ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተናል ብለዋል። ‎‎ውይይታቸውም ኢንቨስትመንትን፣ ቱሪዝምን፣ የታዳሽ ኃይል አጋርነትን ማስፋፋት እና ወደ ኮፕ 32 በሚደረገው ጉዞ ላይ ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ገልጸዋል። በተጨማሪም በማሌዢያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት፣ ምርታማነት እና የአምራች ዘርፍ ተሞክሮዎችን መውሰድ በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መምከራቸውን አስታውቀዋል። ‎‎ኢትዮጵያና ማሌዢያ ጠንካራ የኢኮኖሚ አጋርነት ለመመስረት የሚያስችል ከፍተኛ አቅም አላቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በክህሎት እና በዘላቂ ልማት ማዕቀፎች አዳዲስ ዕድሎችን የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር የዲጂታል ግብር ክፍያ ሥርዓት ጀመረ
Sep 12, 2026 69
ሰመራ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦የአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር የዲጂታል ግብር ክፍያ ሥርዓት ጀመረ። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሰመራ ሎጊያ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር አህመድ ኑርሳሊም፤ የዲጂታል የግብር ክፍያ ሥርዓት ቀልጣፋ አሰራርን ከመዘርጋት ባለፈ ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሚያስችል ዘመናዊ አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።   የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ለብልሹ አሰራር እንዳይጋለጥ እና የግብር መሰወር ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ግብር ከፋዮች ምንም አይነት እንግልት ሳይገጥማቸው ባሉበት ሆነው የሚከፍሉበት ስርአት መዘርጋቱ አስደሳች መሆኑን ተናግረዋል። ግብር ከፋዮች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና በቴሌብር አማራጮች ባሉበት ሆነው ግብራቸውን በመክፈል ከእንግልት በጸዳ መልኩ ሃላፊነታቸውን በቀላሉ መወጣት ያስችላቸዋል ብለዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኀላፊ ኡመር ኑር እና ሌሎችም የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
የመንግስታዊ አገልግሎቶችን በማዘመን የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል 
Sep 10, 2026 275
ድሬዳዋ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመንግስታዊ አገልግሎቶችን በማዘመን የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ገለጹ። ጳጉሜን 5 "የነገ ቀን" በሚል ስያሜ በድሬዳዋ አስተዳደር በፈጠራና በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተመዘገቡ እምርታዎችን የሚያመላክት የፓናል ውይይትና በአውደ ርዕይ ተካሂዷል።   ከንቲባ ከድር ጁሃር በወቅቱ እንደተናገሩት፣ የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን ተደራሽ በማድረግ የነገዋን ታላቅ አገር የመገንባቱ ጉዞ በተጨባጭ ውጤቶች እውን እየሆነ ነው። የተሻለች እና የበለፀገች አገር ለትውልድ ለማስረከብ በየደረጃው የሚደረገው ርብርብ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ከንቲባው ተናግረዋል። በተለይ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎትን የጨበጠ የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኛ በመገንባት ፈጣንና ቀልጣፋ የመንግስት አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ የነዋሪውን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እየተመለሰ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው አንድ ዓመት በከተማ አስተዳደሩ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እየተሰጡባቸው ባሉ አከባቢዎች አዎንታዊ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል። በአስተዳደሩ ዲጂታል የአሰራር ሥርዓትን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች፣ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እና በግል ተቋማት የተጀመሩ የፈጠራና የቴክኖሎጂ የምርምር ሥራዎች የነገዋን ታላቅ አገር ለመገንባት መደላድል እየፈጠሩ ይገኛሉ ብለዋል።   በድሬዳዋ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ከሙስና የፀዳ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋይ እርካታን ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል። የነገ ቀን በድሬዳዋ ሲከበር ከመድረክ በተጨማሪ በአረጋዊያን መጦሪያ ማዕከል ለሚገኙ አቅመ ደካሞች ከንቲባው ማዕድ ያጋሩ ሲሆን የድሬዳዋ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራርም ተጎብኝቷል።   በስነስርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ አብዲ ሙክታር፣ በብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ፣ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ አገልግሎት አሰጣጥና የሥራ ዕድል እያሰፋ ነው
Sep 10, 2026 218
ጅግጅጋ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ) ፦ዲጂታል ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ አገልግሎት አሰጣጥን እያቀላጠፈና የሥራ እድልን እያሰፋ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን ገለጹ። የጳጉሜን 5 "የነገ ቀን" በሚል ስያሜ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተከበረ ሲሆን በሶማሌ ክልል ደረጃም ቀኑ በጂግጂጋ ከተማ በተለያዩ ዲጂታል የንቅናቄ መርሃ-ግብሮች ተከብሯል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም እንደገለጹት፤ በክልሉ በቴክኖሎጂና በሰው ኃይል ልማት ላይ በስፋት በመስራት ሁለንተናዊ እድገትን በዘላቂነት ለማስመዝገብ እየተሰራ ነው። በተለይ ዲጂታል አገልግሎትን በማስፋፋት ለአገልግሎት አሠጣጥ፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለክልሉ የኢኮኖሚ አቅም መጠናከር ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ አበረታች ውጤቶች ተገኝቷል ብለዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያን ማረጋገጥ በቴክኖሎጂ፣ በፋይናንስ፣ በትራንስፖርትና በሌሎችም ዘርፎች አሰራርን በማዘመን ለቀጣይ ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለውም አስረድተዋል።   ለዚህም ስኬት የተቋማት የማስፈጸም አቅምን መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፣ በክልሉ ተቋማትን በቴክኖሎጂ አቅርቦትና በሰው ኃይል የማደራጀት ሥራው ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል። ለአብነትም በክልሉ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማቀላጠፍ 13 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች መገንባታቸውን ጠቁመዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት መንግሥት ለዲጂታል መሠረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ የሠጠው ልዩ ትኩረት የነገን የሀገሪቱን አድገት ለማፋጠን የሚያግዝ ነው። በዲጂታል ዘርፍ የኢትዮ ኮደርስ፣ የስታርትአፕ እና የዲጂታል ክህሎት ንቅናቄዎች የዜጎችን አቅም በመገንባት ረገድ ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ ይገኛሉ ሲሉም ገልጸዋል የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አሊ በበኩላቸው እንዳሉት ፤ በክልሉ የዲጂታልና የፈጠራ ክህሎትን ለማዳበር ዘርፈ ብዙ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።   በተለይም በክልሉ በስፋት እየተሰጠ ያለው የ“ኢትዮ ኮደርስ” ሥልጠና የወጣቶችን ቴክኖሎጂ የመጠቀም አቅም በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ቴክኖሎጂን ጥቅም ላይ በማዋል የመንግሥትን አገልግሎቶች ለማዘመን ፣ የስራ ዕድል ለመፍጠርና የሀገርን ልማት በማፋጠን በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው አስገንዝበዋል።   በጅግጅጋ ከተማ በተካሄደው በዚህ መርሃ - ግብር ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
የቴክኖሎጂ ልማትና ተጠቃሚነትን የማጠናከር ጉዳይ የነገ መዳረሻን ለመወሰን የሚያስችል ቁልፍ ተግባር ነው
Sep 10, 2026 131
ባህርዳር ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ የቴክኖሎጂ ልማትና ተጠቃሚነትን የማጠናከር ጉዳይ የነገ መዳረሻን ለመወሰን የሚያስችል ቁልፍ ተግባር መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በተገኙበት ተከብሯል።   በመርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የቴክኖሎጂ ልማትና ተጠቃሚነትን የማጠናከር ጉዳይ የነገ መዳረሻን ለመወሰን የሚያስችል ቁልፍ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የዛሬ ችግሮቻችን በጋራ በመፍታት የነገውን መዳረሻችንን የምንተልምበት ጊዜው አሁን ነው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ በተለይም ቴክኖሎጂን መፍጠር፣ በመቅዳትና በስፋት መጠቀም ይገባናል ብለዋል። በተጨማሪም ማህበረሰባዊ ካፒታልን፣ ገንዘብን፣ የአካባቢ ጸጋን በማልማት ጥቅም ላይ የማዋል ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ተናግረዋል።   የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ባንችዓምላክ ገብረማርያም፤ የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ግንባታን ዕውን በማድረግ ነገን የተሻለ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ ትግበራዎች ውስጥ አንዱ የሆኑው የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለዚህ ጥሩ ማሳያ መሆኑን አንስተው ይበልጥ የማስፋትና ተደራሽነቱን የማብዛት ስራ ይሰራል ብለዋል።
ስፖርት
በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ
Sep 12, 2026 81
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ):- በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የመጀመሪያ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሱዳኑን ሂላል አል-ሳሂልን 2 ለ 1 አሸንፏል። በድሬዳዋ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ካርሎስ ዳምጠው በ50ኛው እና በ56ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥሯል። ኢንሳ ሰኢድ ለሂላል አል-ሳሂል ጎሉን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሁለቱ ቡድኖች በድምር ውጤት ሶስት አቻ መሆናቸውን ተከትሎ ጨዋታው ወደ መለያ ምት አምርቷል። በዚህም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በመለያ ምት 4 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ሁለተኛ ዙር ማጣሪያ አልፏል። ወልዋሎ በሁለተኛው ዙር ከዛንዚባሩ ኬኤምኬኤም እና ከሊቢያው አል አህሊ ትሪፖሊ አሸናፊ ጋር ይጫወታል። አል አህሊ ትሪፖሊ በመጀመሪያው ጨዋታ 3 ለ 0 ያሸነፈ ሲሆን የመልሱ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ ይደረጋል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአህጉራዊ መድረክ ሲሳተፍ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የውድድሩ ተሳትፎውን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉን ተከትሎ ነው።
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከሂላል አል-ሳሂል፤ የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የማጣሪያ መልስ ጨዋታ
Sep 12, 2026 111
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ):- በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የመጀመሪያ ቅድመ ማጣሪያ ዙር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የመልስ ጨዋታውን ዛሬ ከሱዳኑ ሂላል አል-ሳሂል ጋር ያከናውናል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከቀኑ 10 ሰዓት በድሬዳዋ ስታዲየም ይካሄዳል። ሁለቱ ክለቦች ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በሩዋንዳ በሚገኘው ኪጋሊ ፔሌ ስታዲየም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የ2 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል። ዋሊድ አል-ሻላ እና ፋሪስ ሞሂ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ካርሎስ ዳምጠው ለወልዋሎ ጎሏን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከሜዳው ውጪ ወሳኝ ጎል አስቆጥሮ ተመልሷል። በአህጉራዊ መድረክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተሳተፈ የሚገኘው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ጨዋታ በተለይም በመጀመሪያው አጋማሽ ጥሩ የማጥቃት እንቅሰቃሴ አድርጓል። በሁለተኛው አጋማሽ ቡድኑ በተጋጣሚው ብልጫ የተወሰደበት ሲሆን ፋሪስ ሞሂ የማሸነፊያውን ጎል ያስቆጠረው በዚሁ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ነው። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ጨዋታ ከአንድና ከዚያ በላይ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ያሸጋግረዋል። ቡድኑ በጨዋታው የግድ ግብ የሚያስፈልገው በመሆኑ የጎል እድሎችን በሚገባ መጠቀም ይኖርበታል። ተጋጣሚው ሊከተለው የሚችለውን የመልሶ ማጥቃት እና የክንፍ መስመር እንቅስቃሴ መግታት ይጠበቅበታል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈ በሁለተኛ ዙር ከዛንዚባሩ ኬኤምኬኤም እና ከሊቢያው አል አህሊ ትሪፖሊ አሸናፊ ጋር የሚጫወት ይሆናል።
የዕለቱ ተጠባቂ ጨዋታዎች: አርሰናል ከሰንደርላንድ፣ ቼልሲ ከሁል ሲቲ እና ሊቨርፑል ከፉልሃም
Sep 12, 2026 123
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ይጀመራል። በዕለቱ ሰባት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት አራት ሰዓት ላይ ሰንደርላንድ ከአርሰናል በስታዲየም ኦፍ ላይት ይጫወታሉ። ባለሜዳው ሰንደርላንድ ከሶስት ጨዋታዎች አራት ነጥብ በመሰብሰብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። የወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ሶስቱንም ጨዋታዎች በማሸነፍ በዘጠኝ ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ሁለቱ ክለቦች በሊጉ ሲገናኙ የአሁኑ ለ35ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 34 ጨዋታዎች አርሰናል 20 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ሰንደርላንድ ያሸነፈው በሶስት አጋጣሚዎች ነው። በቀሪ 11 ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ሰንደርላንድ አርሰናልን ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ ያሸነፈው እ.አ.አ በ2009 ነው። አርሰናል ዛሬ ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ከማንችስተር ሲቲ ይረከባል። ሁለቱ ቡድኖች ባለፈው የውድድር ዓመት በስታዲየም ኦፍ ላይት ባደረጉት የሊግ ጨዋታ ሁለት አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው።   በሌላኛው መርሐ ግብር ቼልሲ በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም ሁል ሲቲን ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ያስተናግዳል። ቼልሲ በስድስት ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። በሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር በአርሰናል የ2 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል። አዲስ አዳጊው ሁል ሲቲ ከሶስት ጨዋታዎች ሰባት ነጥብ በመሰብሰብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ባለሜዳው ቼልሲ ከሽንፈቱ በማገገም ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ ይጫወታል። በአንጻሩ በሊጉ ጠንካራ ጅማሮ ያደረገው ሁል ሲቲ ለተጋጣሚው ፈተና ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። ሊቨርፑል ከፉልሃም ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።   ከሶስት የሊግ ጨዋታዎች አምስት ነጥብ ያገኘው ሊቨርፑል በአምስት ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። በሶስተኛ ሳምንት ኤፕስዊች ታውንን 2 ለ 0 በመርታት የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል። በአንጻሩ በሶስቱም የሊጉ ጨዋታዎች ሽንፈት ያስተናገደው ፉልሃም ያለ ምንም ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ጨዋታው ሊቨርፑል ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ፉልሃም የመጀመሪያ ሶስት ነጥቡን ለማግኘት የሚያደርጉት ነው። አስቶንቪላ ከኖቲንግሃም ፎረስት፣ ክሪስታል ፓላስ ከኤፕስዊች ታውንና ቦርንማውዝ ከብሬንትፎርድ በተመሳሳይ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከኤቨርተን በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም ይጫወታሉ።  
ማንችስተር ዩናይትድ እና ባየር ሙኒክ  ድል ቀንቷቸዋል
Sep 11, 2026 162
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ትናንት ማምሻውን አራት ጨዋታዎች ተካሄደዋል። በኦልትራፎርድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ሳባህን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል። ማትያስ ኩንያ፣ ብሩኖ ፈርናንዴዝ፣ ቤንጃሚን ሼሽኮ እና ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ባለሜዳው ማንችስተር ዩናይትድ ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል። የአዘርባጃኑ ሳባህ በውድድሩ ላይ ሲሳተፍ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። በሌላኛው መርሐ ግብር ባየር ሙኒክ ቦዶ ግሊምትን 5 ለ 0 ረትቷል። ማይክል ኦሊሴ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ጀማል ሙሲያላ፣ ሃሪ ኬን እና አልፎንሶ ዴቪስ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። የጀርመኑ ክለብ በመጀመሪያ አጋማሽ ከተጋጣሚው ፈተና ቢገጥመውም በሁለተኛው ክፍለ ጊዜ ግቦቹን በማስቆጠር ማሸነፍ ችሏል። በሻምፒዮንስ ሊጉ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተሳተፈ የሚገኘው የጣልያኑ ክለብ ኮሞ አርቢ ላፕዚግን 4 ለ 1 አሸንፏል። ሌንስ ስላቪያ ፕራግን 3 ለ 2 ማሸነፍ ችሏል። ትናንት አስቀድመው በተደረጉ ጨዋታዎች ፊነርባቼ ከሮማ ፣ ፒኤስቪ ከሻካታር ዶኔስክ በተመሳሳይ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የመጀመሪያ ዙር መርሐ ግብር ተጠናቋል። ሁለተኛ ዙር የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም መግቢያ ይካሄዳሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ስኬታማ ሥራ ተከናውኗል
Sep 10, 2026 198
የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር በ2011 ዓም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በይፋ መጀመሩ ይታወቃል። መርሃ ግብሩ እንደ ሀገር ያጋጠሙ በርካታ የዘላቂ ልማት ተግዳሮቶችን የመሬት መጎሳቆል የደንና ብዝሃ ህይወት መጨፍጨፍ፣ የውሃ አካላትን መድረቅና በደለል መሞላት ለመከላከል ታስቦ ወደ ሥራ መገባቱ ይታወቃል። በዚህም በመጀመሪያው ምዕራፍ 50 ቢሊዮን ችግኝ በማህበረሰብ ተሳትፎ ለመትከል ታቅዶ ነበር።   ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት የመርሃ ግበሩ የትግበራ ዓመታት 56 ነጥብ 8 ቢሊዮን ችግኞችን፤ በዚህ ዓመት ብቻ ደግሞ 8 ነጥብ 2 ቢሊዮን ችግኝን በመትከል በዓለም ላይ አዲስ ታሪክ ፅፋለች። አጠቃላይ ከተተከሉ ችግኞች ከ3 ቢሊዮን በላይ የሚሆኑት በአንድ ጀምበር የተተከሉ መሆናቸው በዓለም ላይ ትልቅ የችግኝ ተከላ ሆኖ ተመዝግቧል። ከተተከሉ ችግኞች 60 በመቶ የሚሆኑት የጥምር ደን ግብርና (የፍራፍሬ፣ የቡና፣ የመኖ ዝርያዎች) ሲሆኑ 35 በመቶ የደን ዝርያ ናቸው። ይህ ታላቅ የልማት ድል የተሳካው ከላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እስከ ታችኛው የመንግስት አደረጃጀት ለመርሃ ግብሩ በተሰጠው ቁርጠኛ አመራር ነው። በየዓመቱ ከ25 ሚሊየን በላይ ዜጎች በችግኝ ተከላ ተሳትፈዋል።   እስካሁን በተሠራው ሥራ በየዓመቱ ይፈጸም የነበረው የደን ጭፍጨፋ ከ92 ሺህ ወደ 27 ሺህ ሄክታር እንዲቀንስ አስችሏል። በእርሻ ማሳ የአፈር መከላት በዓመት በሄክታር ከ130 ቶን ወደ 54 ቶን ቀንሷል። አረንጓዴ ዐሻራ በየዓመቱ ወደ ውሃ አካላት የሚገባ የአፈር ደለል ከ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ቶን ወደ 208 ሚሊዮን ቶን ዝቅ እንዲል አስችሏል። በመርሃ ግብሩ ለ2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ወጣቶችና ሴቶች አረንጓዴ ሥራ ተፈጥሮላቸዋል።   በበርካታ አካባቢዎች የፍራፍሬና የደን ክላስተር እየተፈጠረ አርሶ አደሮች የላቀ የኢኮኖሚ አቅም እንዲገነቡ እያስቻለ ነው። ኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት መርሃ ግብር ቀርጻ መተግበር እንደምትችል ትልቅ ተሞክሮ የተወሰደበትና ለዓለም ያሳየችበትም ነው። ከዚህም ባለፈ ሀገራችን ዓለም እየተፈተነችበት ላለው የአየር ንብረት ለውጥ ተግባራዊ መፍትሔ በመስጠት ምሳሌ መሆኗን ያሳየችበት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ማጠናቀቂያ የችግኝ ተከላ አካሄዱ
Sep 10, 2026 161
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ):- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ማጠናቀቂያ የችግኝ ተከላ አካሂደዋል። ‎የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እንደገለጸው በዘንድሮው ዓመት «ተስፋን እንትከል» በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የነበረውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ማጠናቀቂያ ነው የችግኝ ተከላ ያካሄዱት።   የ2018 ዓ.ም የችግኝ ተከላ መጠናቀቅን ስናበስር የተተከለው እያንዳንዱ ችግኝ የሕብረታችን፣ የሕዳሴያችንና የዘላቂ እድገታችን ሕያው ምልክት መሆኑን በማስታወስ መሆኑንም አስታውቋል። ‎የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ‎በጽኑ አንድነታችንና በጋራ ጥረታችን የታነጸች፣ የበለጸገችና ብሩህ ኢትዮጵያን ለማየት ሙሉ ተስፋ ሰንቀን ወደፊት እንገሰግሳለን ሲልም መልእክት አስተላልፏል።
የአየር ንብረት ለውጥ በማኅበረሰብ ጤና ላይ ሊያሳድር የሚችለውን ተፅዕኖ ለመከላከል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Sep 9, 2026 221
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦የአየር ንብረት ለውጥ በማኅበረሰብ ጤና እና ስነ-ምግብ ላይ ሊያሳድር የሚችለውን ተፅዕኖ ለመከላከል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ሀይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር በጤና እና በስነ-ምግብ መጠበቅ ላይ ያለውን ሚና በተመለከተ የምርምር ጉባኤ የዘርፉ ተዋናዮች በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል። ዶክተር መሳይ ሀይሉ በመድረኩ እንደተናገሩት፤ ከተለያዩ የህብረተሰብ ጤና ፈተናዎች መካከል ከውሃ ጋር በተገናኘ የሚፈጠሩ የጤና ችግሮች እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን ለመሻገር እየወሰደቻቸው ያሉ የፖሊሲ እርምጃዎች ትልቅ ሚና አላቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን መትከሏ ተስማሚ የአካባቢ አየር ንብረት እንዲኖር አድርጓል ብለዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ አረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማበረታታት የወሰደቻቸው የፖሊሲ እርምጃዎች የአየር ብክለትን በመቆጣጠር የማኅበረሰብን ጤና ለመጠበቅና ስነ-ምግብን ለማሻሻል የራሳቸው አበርክቶ እንዳላቸው ገልጸዋል።   ኢንስቲትዩቱ በአረንጓዴ ልማት ላይ የሚሰሩ ስራዎችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በማጥናት የደን ልማትና ንጹህ መጓጓዣ የመፍጠር እርምጃዎች ከአየር ንብረት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን የበሽታ ጫናዎች እንደሚቀንሱ፣ የአየር ጥራትን እንደሚያሻሽሉ እና የስነ-ምግብ ክትትልን እንዴት እንደሚያጠናክሩ በጥናት የማረጋገጥ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ኢንስቲትዩቱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚሰሩ ስራዎች በጤናው ዘርፍ ያላቸውን አበርክቶ በምርምር ስራዎች ለመፈተሽና በቀጣይ በሚሰሩ ተግባራት ላይ ከተለያዩ ተቋማት ጋር ያለውን የትብብር ስራ ለማጠናከር መድረኩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፈጠነ ተሾመ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ተቋሙ በመረጃ ላይ የተመሰረቱ የአየር ፀባይ ትንበያዎችን በመተንተንና በማደራጀት ለጤናው ዘርፍና ለልዩ ልዩ ጥቅሞች እንዲውሉ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተገናኙ መረጃዎችን በመለዋወጥ የማህበረሰብ ጤና እንዲጠበቅ ትብብሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ለበሽታ ክትትል፣ ለአደጋ ዝግጁነት እና ለቅድመ ማስጠንቀቂያ የሚረዱ የአየር ንብረት መረጃዎችን በወቅቱና በቀጥታ ለማድረስ ተግቶ ይሰራል ነው ያሉት።
የኢትዮጵያውያን ኅብር በውጤት የተገለጠበት - አረንጓዴ አሻራ  
Sep 9, 2026 260
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ ባለፉት አሥርት ዓመታት የደን መመናመን፣ የአፈር መሸርሸር፣ የለም መሬት እየቀነሰ መምጣት እና ተደጋጋሚ ድርቅን ጨምሮ እጅግ አስቸጋሪና ተደራራቢ የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ይገጥሟት ነበር። ይህ የስነ-ምህዳር መዛባት በሚሊዮን የሚቆጠሩ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮችን ህይወትና የምግብ ዋስትና አደጋ ላይ ጥሎት ቆይቷል። በተለይም በቆላማ እና ከፊል አርብቶ አደር በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች የውሃ ምንጮች መድረቅ እና የግጦሽ መሬቶች መውደም ሰብአዊ ህይወቶችንና የቁም እንስሳትን ለአደጋ አጋልጧል። የብዝሃ ህይወት መመናመን ሌላኛው ፈተና ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን፣ ይህ የተፈጥሮ ሀብት መመናመን በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት ጎዳና ላይ ትልቅ ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል። ኢትዮጵያ ይሄን የአየር ንብረት ለውጥ በዘላቂነት ለመከላከል እና የተፈጥሮ ሀብትን ለመጠበቅ ከቃል ያለፈ የተግባር ስራ ከጀመረች ዓመታት ተቆጥረዋል። የዚህ ሀገራዊ ስራ አበይት መገለጫ ከሆኑ ብሔራዊ ኢኒሼቲቮች መካከል “አረንጓዴ አሻራ” ተጠቃሽና ግንባር ቀደም መርሃ ግብር ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የደን መመናመንን ለመግታትና ሥነ-ምህዳርን ለመመለስ የተጀመረ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ስራ ዛፍ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያውያን በአንድነትና በህብር በመቆም በጋራ የሰሩበት ታላቅ ህብረተሰባዊ አቅም የታየበት ማረጋገጫም ሆኗል። ሀገሪቱ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን ታላቁን የዓለም አቀፍ አየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ 32) በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እንድታስተናግድ መመረጧ፣ በአረንጓዴ ልማት ያሳየችው የህብርና የአንድነት ጉዞ ያስገኘው ትልቅ ዓለም አቀፋዊ ድል ነው። በአረንጓዴ አሻራ ስኬት ትልቁ መገለጫ የህዝቦች የጋራ ትብብር እና ተደጋግፎ መስራት መሆኑን በተግባር ለማሳየት ተችሏል። የኢትዮጵያ የደን ሽፋን በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 17.2 በመቶ በጥቂት ዓመታት ውስጥ ማለትም በ2017 ዓ.ም ወደ 23.6 በመቶ ማደግ ችሏል። እስካሁን ከ54 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በአንድነት በመሳተፍ ለአየር ንብረት ተጋላጭ የነበሩ አካባቢዎች አረንጓዴ ለብሰው እንዲለወጡ አድርገዋል። በብራዚል ቤለም በተካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን ኢትዮጵያን የኮፕ 32 አስተናጋጅ አድርጎ በሙሉ ድምፅ መምረጡ የህብር እና የአንድነት ውጤት ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬት የተለካው ችግኝ በመትከል ብቻ ሳይሆን፣ ህዝብና መንግስት በህብር ተክሎ የማሳደግና የመንከባከብ ባህልን በማዳበር ሲሆን የተተከሉ ችግኞች የመጽደቅ ምጣኔ ከ85 በመቶ በላይ ሆኗል። ይህ ሂደት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከአቮካዶ፣ ማንጎና ፓፓያ የመሳሰሉ የፍራፍሬ ችግኞች መተከል ጋር ተያይዞ የግብርና ምርታማነትን ያሳደገ ሲሆን፣ ለብዙ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል። መርሃ-ግብሩ ከደን ዛፍ ችግኝ ባለፈ የምግብ እና የከተማ ውበት መሰረት የሆኑትንም ያካተተ በመሆኑ ውጤቱን የላቀ አደርጎታል። የግብርና ምርታማነት እንዲጨምርም ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት የተደረገ የአካባቢ ጥበቃ ስራ ብቻ ሳይሆን፣ ሕዝቦች በአንድነትና በህብር ሲሰለፉ ሀገራቸውንና መልክዓ ምድራቸውን መቀየር እንደሚችሉ ለዓለም ያሳዩበት ታላቅ ማረጋገጫ ነው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አፍሪካ በዓለም ፊት ቦታ ለማግኘት አትማጸንም ፤ ይልቁንም የሚገባትን ስፍራ በባለቤትነት እየያዘች ነው
Sep 9, 2026 233
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ):- አፍሪካ በዓለም ፊት ቦታ ለማግኘት አትማጸንም ፤ የሚገባትን ስፍራ እና ክብር በራሷ እያረጋገጠች ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ቀን ዛሬ እየተከበረ ይገኛል። የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ቀኑን በማስመልከት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት ቀን እ.አ.አ በ1999 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለመተካት ይፋዊ ውሳኔ የተላለፈበት የሰርጥ ድንጋጌ (Sirte Declaration) የሚታወስበት እንደሆነ ገልጸዋል። በዚያን ወቅት የአፍሪካ መሪዎች አህጉራዊ ትስስርን ለማፋጠን እና የአፍሪካን ድምጽ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ለማድረግ የአፍሪካ ህብረትን ለመመስረት ወሳኝ እና ታሪካዊ እርምጃ የወሰዱበት ምዕራፍ ነው ብለዋል። የዘንድሮው የአፍሪካ ህብረት ቀን ለአህጉሪቱ እጅግ ልዩ ትርጉም ባለው ወቅት ላይ እየተከበረ እንደሚገኝ አውስተዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ የአፍሪካን እውነተኛ ቁመና እና ትክክለኛ መጠን የሚያሳይ የዓለም ካርታ አጠቃቀምን የሚደግፍ፣ በአፍሪካ መሪነት የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ አፅድቋል። በቶጎ ሃሳብ አመንጪነትና በአፍሪካ ህብረት ድጋፍ እውን የሆነው ይህ እርምጃ ከቀላል የካርታ ማስተካከያ በላይ ትርጉም አለው ብለዋል ሊቀ መንበሩ። አፍሪካ በዓለም ፊት እንዴት እንደምትታይ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን እና አፍሪካ ራሷን የምትገመግምበትንና የምታሳይበትን ትርክት ራሷ መቅረጽ እንዳለባት አበክሮ የሚያስታውስ ነው። ይህ ውሳኔ አፍሪካ በዓለም ፊት በምን መልኩ መታየት እንዳለባት ከማሳየቱም በላይ፤ አፍሪካ ራሷን የምትመዝንበትንና እውነታዋን ለዓለም የምታሳይበትን ትርክት በራሷ መቅረጽ እንዳለባት በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን ነው ያነሱት። የአፍሪካ እጣ ፈንታ የሚወሰነው በአፍሪካውያን የራሳቸው እይታ ነው። አፍሪካን በእውነተኛ ቁመናዋ፣ኃይሏ እና አቅሟ የምንመለከትበት ጊዜ አሁን ነው ብለዋል። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር አያይዘውም ካርታውን የማስተካከል እርምጃ አፍሪካ ወደ ላቀ የጋራ ራዕይ የምታደርገው አህጉራዊ ጉዞ አካል መሆኑን አንስተዋል። ይህም በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠና (AfCFTA) አማካኝነት የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከርን፣ ሰላም እና ፀጥታን ማረጋገጥን፣ ዘላቂ ልማትን እውን ማድረግን እና በዓለም አቀፍ ውሳኔ ሰጪ አካላት ውስጥ የአፍሪካን ተሳትፎ ማሳደግን እንደሚያካትት በዝርዝር አስረድተዋል። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የተሳሰረች፣ የበለጸገች እና ሰላማዊት አፍሪካን ለመገንባት የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ሰላም እና ፀጥታን ማረጋገጥ፣ የኢኮኖሚ ትስስርን በማፋጠን እና የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ተሰሚነት መጨመር የአፍሪካ ህብረት ቀዳሚ ትኩረቶች ናቸው ብለዋል። አፍሪካ በዓለም ፊት እውቅና ለማግኘት አትለምንም፤ ይልቁንስ በዓለም አቀፍ መድረክ የሷ የሆነውን ትክክለኛ ስፍራ በራሷ ባለቤትነት እየያዘች ነው። አሁን የሚጠበቅብን ይህንን ጠንካራ እምነት ወደ ህብረት፣ ሀብትና ብልጽግና፣ ሰላም እና ተደማጭነት መለወጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ሊቀመንበሩ አፍሪካ የምታስመዘግበው እድገት በዓለም አቀፍ መድረኮች በሚኖራት ውክልና ብቻ ሳይሆን፣ በዜጎቿ ላይ የኑሮ ጥራት መሻሻል ጭምር መለካት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል። በዚህም መሰረት የአፍሪካ ህብረት የ2026 ዓመት ትኩረቱን በዘላቂ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አገልግሎት ላይ ማድረጉ፣ ህብረቱ አህጉራዊ ራዕዮችን ከዕለት ተዕለት የዜጎች ህይወት ጋር ለማያያዝ ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አመልክተዋል። በአፍሪካ ህብረት ቀን አከባበር አባል ሀገራት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የአፍሪካ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ሴቶች እና ወጣቶች ተባብረው ይበልጥ የተሳሰረች፣ በራሷ አቅም የምትተማመን እና የራሷን እጣ ፈንታ በራሷ መወሰን የምትችል አፍሪካን እንዲገነቡ ሊቀመንበሩ ጥሪ አቅርበዋል። የምንፈልጋት አፍሪካ የሚለውን አህጉራዊ ራዕይ እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ እና የሰርት ድንጋጌ ለቀጣዩ የአፍሪካ ትውልድ ዘላቂ የትምህርት እና የዕድገት መሰረት ሆኖ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የነገዋ አፍሪካ በካርታ ላይ ብቻ የተሻለ ውክልና ያላት ብቻ ሳትሆን፤ በዓለም አቀፍ መድረክ ሉዓላዊነቷ የጸና፣ ጠንካራ ውስጣዊ አንድነት ያላት፣ ለህዝቦቿም ዘላቂ ብልጽግናን የምታጎናጽፍ አህጉር መሆን ይኖርባታል ነው ያሉት። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር ለመላው አፍሪካውያን እና በውጭ ሀገር ለሚገኙ የአፍሪካ ዳያስፖራዎች ሰላማዊ እና የትብብር መንፈስ የተሞላበት የአፍሪካ ህብረት ቀን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ አጋርነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Sep 4, 2026 498
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 29/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን እና ሁሉን አቀፍ ትብብራቸውን የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ውይይቱ በአፍሪካ ህብረትና አሜሪካ መካከል ያለውን ለረጅም ጊዜ የቆየ አጋርነት ማጠናከር እና በአህጉሪቱ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር የአፍሪካና አሜሪካን ትብብር ታሪካዊ መሆኑን አውስተው በህብረቱ፣ በአባል ሀገራት እና በአሜሪካ መካከል የሁለቱንም ወገኖች ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ ጠንካራ አጋርነት መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል። በምስራቅ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሱዳን እየተደረጉ ላሉ አፍሪካ መር የሰላም ጥረቶች አሜሪካ እያደረገች ላለው ገንቢ አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያ በበኩላቸው አፍሪካ አሜሪካ ቀዳሚ ትኩረት የምትሰጣት አህጉር እንደሆነች ገልጸዋል። የጋራ ፍላጎቶችንና ግቦችን ከህብረቱ ኮሚሽንና ከአባል ሀገራት ጋር በመሆን ለማሳካት ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በዲፕሎማሲ፣ እንዲሁም በሰላምና ጸጥታ ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባም አመልክተዋል። በውይይቱ ላይ በሱዳን ጉዳይ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የሰብአዊ እርዳታ ያለ ገደብ እንዲገባ እና በሲቪሎች የሚመራ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመር አጽንዖት ተሰጥቷል። በአፍሪካ ባለቤትነት የሚመሩ የሰላም ጥረቶች እና አሜሪካ የምትደግፋቸው የሰላም ሂደቶች በተቀናጀ መልኩ ለመተግበር ከስምምነት ላይ ተደርሷል። በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመሰረተ ልማት እና በሰላም መስኮች የሁለቱን ወገኖች ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ የትብብር መስኮች ተገምግመዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ህብረትና በአሜሪካ ስትራቴጂክ ኢንቨስትመንት ማዕቀፍ ውስጥ የተደረጉ ስምምነቶችን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። በሊቢያ ጉዳይ ዘላቂ የፖለቲካ መፍትሄ ማግኘት እንደሚያስፈልግም ተነስቷል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር እና ረዳት ሚኒስትሩ የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና የትብብር አድማሱን ለማስፋት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 1804
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 1461
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
ሐተታዎች
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦች የመቻል ተምሳሌት 
Sep 9, 2026 226
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦች የመቻል ተምሳሌት መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም የኢትዮጵያውያን የጋራ ቃል ኪዳን የታሰረባት ታሪካዊ ክስተት ናት። ዕለቷም የዓባይን የሺሕ ዘመናት ገደብ የሌለው ጉዞ በጉባ ተራሮች ግርጌ ልጓም ለማበጀት የታሰረች ቀለበት ሆና ተመዝግባለች። ኢትዮጵያውያን ቃል ኪዳናቸውን ባሰሩ ማግስት የግብፅና ሌሎች ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጩኸትና የጥፋት ሴራ በግልጽ መታየት ጀመረ። በተለይም ግብፅ ኢትዮጵያ ውስጣዊ መረጋጋት እንዳይኖራት የውስጥ ታጣቂዎችን ከመደገፍ ጀምሮ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በራፍ ጭምር የሀሰት ክሶችን እስከማሰማት የደረሰ የሺሕ ዘመናት ዓባይን በብቸኝነት የመጠቀም አባዜዋን አንጸባርቃለች። ትብብርን ከፅናት አሰናስለው የቀጠሉት ኢትዮጵያውያን ለአሥራ አራት ዓመታት የታላቁ ሕዳሴ ግድብን የማደናቀፍ የታሪካዊ ጠላቶችን ሴራ በጋራ በመመከት ለፍጻሜ አብቅተውታል። የሀገርን ሉዓላዊነት በጽናት የማስከበር የአርበኝነት ተጋድሎን ከዓድዋ ጀግኖች የወረስን እኛ ኢትዮጵያውያን በጉባ ተራሮች ግርጌ በደም፣ በላብ፣ በዕንባና በውኃ ጠብታ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን በዓባይ ላይ አንጸናል።   ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የአዲስ ዓመት ዋዜማም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በማጠናቀቅ ለፍጻሜ በማድረስ አብስሯል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሺሕ ዘመናት የልማት ጥማትን በማርካት የብልፅግና ፍኖት ብስራት ሆኗል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ለሌላ የልማት ዕቅድ ወጋገን የፈነጠቀ የንጋት ሐይቅ ፈጥሯል። ግድቡ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝቦቿ ትብብር ብቻ ያለ አንዳች የውጭ ድጋፍና ብድር ለፍጻሜ መብቃቱም ለአፍሪካውያን የመቻል ትዕምርት ሆኗል። በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ብስራት በጉባ ተራሮች ግርጌ የከተሙ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት መሪዎች የመሰከሩት ጥሬ ሐቅም ይህ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምረቃው ዕለት እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦችን የታሪክ ክብር ያደሰና ለአፍሪካውያን የመቻል ውጤት ነው። በወቅቱም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጎህ ያበሰረ፣ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርና የጋራ ዕድገት መንገድ የጠረገ ፓን-አፍሪካኒዝም ፕሮጀክት መሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ አፍሪካውያን አንጡራ ሀብታቸውን በራሳቸው አቅምና ጥረት በማልማት ታላላቅ የልማት ገድሎችን መፈጸም እንደሚችሉ ያመላከተ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የኩራት ምንጭ መሆኑንም ጠቁመዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር እና የክብር እንግዳ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ የታዳሽ ኃይል ሽግግርን በማፋጠን የአፍሪካውያንን የጋራ ምኞት የሚያሳካ ህያው ምልክት ነው ማለታቸው ይታወሳል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅና ለምረቃ መብቃትም የኢትዮጵያውያንን ለአንድ ሀገራዊ የልማት ርዕይ በጋራ የመቆም ውጤታማነትን በተግባር ለዓለም የገለጠ ፓን-አፍሪካኒዝም ፕሮጀክት መሆኑን መስክረዋል። በዚሁ ወቅት የተገኙት የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጌሌ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዘመናዊው ዓለም የአፍሪካውያን የኩራት ምንጭ የሆነ የልማት ድል መሆኑንና መላውን ዓለም ያስደነቀ የኢትዮጵያ ስኬትና የወዳጆቿ የጋራ ሀብት ነው። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ብሔራዊ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን አስደማሚ የፓን-አፍሪካኒዝም መግለጫ ፕሮጀክት ነው ያሉት ደግሞ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ የታደሙት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ናቸው።   የኢትዮጵያውያን ብሔራዊ ፕሮጀክት የሆነው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት አፍሪካውያን በተባበረ ክንድ አቅማቸውን በመጠቀም የራሳቸውን ዕድል በራሳቸው መወሰን እንደሚችሉ ትምህርት ያስተላለፈ ነው ሲሉም መግለጻቸው ይታወሳል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የምህንድስና ልህቀትም አህጉሪቱ ለብልፅግናዋ የሚረዱና ሁለንተናዊ ለውጥ የሚያመጡ ሁነኛ የልማት ፕሮጀክቶችን በራሷ አቅም የመገንባት ብቃት እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ የተገኙት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ እንደተናገሩት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አህጉራዊ ትብብርና ግንኙነትን የሚያጠናክር የወንድማማችነት ምልክት ነው። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁላችንንም ተጠቃሚ የሚያደርግ የጋራ ጉዳያችን ነው በዚህም ዕድለኞች ነን ሲሉ መግለጻቸውም ይታወሳል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ "ለእኛ እንደ አንድ ፕሮጀክት ሳይሆን ሀላፊነትን የምንጋራበት ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ አፍሪካውያን ከተባበርን ስኬቶችን ማስመዝገብ እንደምንችል ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። የላይኛውና የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት መበልጸግ የሚችሉት በጋራ እንደ አንድ ማህበረሰብ በመስራት ነው። ውሃና ሌሎች ተፈጥሯዊ ሀብቶች በድንበር የተወሰኑ ሳይሆኑ የወደፊት እጣ ፈንታችንን የሚወስኑ ናቸው ብለዋል።   የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት በበኩላችው እንደሚሉት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአንድነት እና የመስዋዕትነት ምልክት ነው። ግድቡ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን የአንድነትና የመስዋዕትነት ምልክት ነው፡፡ የግድቡ ግንባታ እውን መሆን ህዝብ ከተባበረ እና ለአንድ ዓላማ በአንድነት ከቆመ ምን መስራት እንደሚችል ማሳያ መሆኑን ነው ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህም ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የኩራት ምንጭ ነው ማለታቸው ይታወሳል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ግድቡ የኃይል ፍላጎትን ከማሳካት ባለፈ ለልጆቻችን የምንመኘውን የበለጸገ ሀገርና አህጉር ለማስረከብ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ይህ በታሪክ ድርሳናት ሰፊውን ድርሻ የሚይዘው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት የኢትዮጵያዊያን የቃል ኪዳናቸው ማህተም ሆኖ ለዘላለም ይኖራል።
የፀጥታና ደህንነት ተቋማት በመጠናከራቸው ኢትዮጵያን የማትበገርና የጸናች ሀገር አድርጓታል
Sep 8, 2026 296
የፀጥታና ደህንነት ተቋማት በመጠናከራቸው ኢትዮጵያን የማትበገርና የጸናች ሀገር አድርጓታል ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን፣ ሰላሟንና የሕዝቦቿን ደህንነት ለማስጠበቅ ባለፉት ዓመታት በጸጥታና ደህንነት ዘርፍ በተቋማዊ አደረጃጀት፣ በሕግ፣ በሙያዊ አቅም ግንባታ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በተቀናጀ አሠራር ያካሄደቻቸው ሪፎርሞች የጸጥታ አቅሟን እንድታሳድግ አስችለዋል። በዚህም የፖሊስና የመረጃ ተቋማት የሚመሩበት የሕግ ማዕቀፍና ተቋማዊ አደረጃጀቶችን ከማጠናከር ባሻገር፣ ተቋማቱ የዘመኑን የጸጥታ ተግዳሮቶች መመከት የሚያስችላቸውን አቅም እንዲገነቡ ተደርጓል። በመከላከያ ዘርፍም የሠራዊቱን አደረጃጀትና የማድረግ አቅም ማጎልበት፣ የቴክኖሎጂ አቅሙን ማጠናከር የሪፎርሙ የትኩረት አቅጣጫዎች ነበሩ። በዚህም የምድር ጦርን ጨምሮ የአየር ኃይልና የባሕር ኃይል አቅምን ማጠናከር እንዲሁም ከዘመናዊ የሰራዊት አሠራር ጋር የሚሄድ የወታደራዊ አቅም መገንባት በዚሁ አቅጣጫ ተካትቷል።   በቅርቡ በሃዋሳ በተካሄደ የኮማንዶ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ ኢትዮጵያ የሀገሪቱን ደህንነት ከማስጠበቅ ባለፈ በቀጣናውና በአፍሪካ ሰላምና ብልጽግና ላይ አስተዋፅዖ ማድረግ የሚችል በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ኤሊት የጦር ኃይል ለመገንባት እየሠራች ነው። በምድርና በአየር የነበረውን ወታደራዊ ሥልጠና ወደ ባሕር ማስፋፋትን ጨምሮ፣ የጦር ኃይሉን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማጠናከርና የተለያዩ የውጊያ አቅሞችን ማሳደግ የሠራዊቱን ዘመናዊነት ለማረጋገጥ ከተወሰዱ አቅጣጫዎች መካከል መሆናቸውን መጠቆማቸው ይታወሳል። በተመሳሳይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ በ45ኛው የፅናት ኮርስ የኮማንዶ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ እንዳሉት፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የተጠናከረ ወታደራዊ አቅም እንዲኖረው ተሰርቷል። የቴክኖሎጂ ግኝቶችን የታጠቅንበት ዘመን ላይ ነን ያሉት ፊልድ ማርሻሉ፣ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ውስጥና የውጭ ጠላቶች እንደማይችሏት ገልጸዋል። የጸጥታ ተቋማት በተናጠል ከመሥራት ይልቅ በቅንጅት እንዲሠሩ ማድረግም በሪፎርሙ የተሰጠው ትኩረት ሌላው አቅጣጫ ነው።   የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፣ የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮችና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች ሀገራዊ የጋራ የፀጥታ መድረክ ላይ እንደገለጹት፣ የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ የጸጥታ ተቋማት በጋራ በማቀድ፣ በመቀናጀትና ልምድ በመለዋወጥ የጋራ የጸጥታ ተልዕኮዎችን የሚያከናውኑበት አሠራር ተጠናክሯል። ይህ የተቀናጀ አሠራር በተለያዩ ብሔራዊ ዝግጅቶችና የሀገራዊ ጸጥታ ተልዕኮዎች ወቅት የተቋማትን የጋራ አቅም ለመጠቀም መሠረት መሆኑ በቀደመ ማብራሪያዎች ጠቁመዋል። የሳይበር ደህንነት የሀገራዊ ደህንነት አካል እየሆነ መምጣቱ የሪፎርሙ አንድ አካል እንዲሆን ተደርጓል። በዚህ ረገድ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ አምስተኛው ዙር ብሔራዊ የሳይበር ታለንት የሰመር ካምፕ ማስጀመሪያ መርሃግብር ላይ እንደገለጹት፤ አስተዳደሩ ተቋማዊ አቅሙን በማሳደግ ወሳኝ የመረጃ መሠረተ ልማቶችን ከሳይበር ጥቃቶች ለመጠበቅ የሰው ኃይል ልማት፣ የዝግጁነት አቅምና የተቋማት ትብብርን ማጠናከር ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።   የሳይበር ደህንነት የሀገሪቱን ዲጂታል ሽግግር ለማረጋገጥ ወሳኝ በመሆኑ በዘርፉ ብቁ የሰው ኃይል ማፍራትና የተቋማትን ዝግጁነት ማጠናከር ቀዳሚ ትኩረት ነው ብለዋል። በአጠቃላይ በሀገሪቱ የጸጥታና ደህንነት ዘርፉ የተከናወኑት ሪፎርሞች የጸጥታና ደህንነት ሥርዓቱን በተቋማዊ አደረጃጀት፣ በሙያዊ ብቃት፣ በቴክኖሎጂና በቅንጅታዊ አሠራር ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፣ ይህም ሀገሪቱ የራሷን የጸጥታ አቅም በማሳደግ ሉዓላዊነቷን፣ ሰላሟንና ብሔራዊ ጥቅሟን በበለጠ አቅም ለማስጠበቅ ያላትን ብቃት አጠናክሯል።
በልጆቿ ፀንታ የኖረች ሀገር
Sep 8, 2026 507
በብርሀኑ ፍቃዱ (ሰቆጣ ኢዜአ) የውጪ ወራሪን በጀግኖች አባቶቻችን ክቡር መስዋዕትነትና በጸና ተጋድሎ በማክሸፍ፣ ኢትዮጵያን በትውልድ ቅብብሎሽ አጽንቶ አሁን ላለንበት ማድረስ ተችሏል። ለአብነትም የጣሊያን ወራሪ ኃይል በጥንት አባቶቻችን ተጋድሎ ሽንፈትን ተከናንቦ መመለሱ ለኢትዮጵያዊያን ድልና ለመላው ጥቁር ህዝብ የነፃነት ፋኖስ ሆኖ ሲዘከር ይኖራል። "የአይቻልም" መንፈስን በ"ይቻላል" ለውጠው ያሳዩት እነዚህ ጀግኖች፣ ለጥቁር ህዝቦች የነፃነት ጮራ የፈነጠቁ፣ እኩልነትን ያበሰሩ፣ የሀገር ፍቅርና ጽናትን ለልጅ ልጆቻቸው ያወረሱ እንዲሁም ታሪክን በወርቅ ቀለም የጻፉ ናቸው። የዛሬው ባለታሪኮቻችን ሻለቃ ባሻ ሞገስ የማነብርሃን እና መቶ አለቃ አበባው ገብረ እግዚአብሔር ለሀገራቸው ሉዓላዊነት መከበር በጽናት ታግለው ያሳለፉትን የተጋድሎ ታሪክ «የጽናት ቀን»ን ምክንያት በማድረግ እንደሚከተለው እናስቃኛችኋለን። በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በሰቆጣ ወረዳ «ቃፋ ሚካኤል» በተባለ መንደር ነዋሪ የሆኑ ሻለቃ ባሻ ሞገስ የማነብርሃን፣ ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ ለ22 ዓመታት ክቡር በሆነው የውትድርና ሙያ ሀገራቸውን አገልግለዋል። "ጀግንነትን፣ አሸናፊነትን እና ለሀገር አንድነት መስዋዕት መክፈልን ከአባቴ ከሻለቃ የማነብርሃን የወረስኩት አኩሪ ታሪክ በመሆኑ፣ እኔም ለሀገሬ ክብር በጽናት ተዋድቄያለሁ" ሲሉ ይገልጻሉ። የውትድርና ሕይወታቸውን በቀብሪ ደሃር ማሰልጠኛ ማዕከል የጀመሩት ሻለቃ ባሻ ሞገስ፤ በዳሎል፣ ምፅዋ፣ ከረን፣ ሙሳቤት፣ ቃሮራ፣ አፋበት፣ ናቅፋ እና በሌሎች የኤርትራ ቆላማና ደጋማ አካባቢዎች የተሰጣቸውን ግዳጅ በጽናት ተወጥተዋል። "የወጣትነት እድሜዬን ክቡር የሆነውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት በመቀላቀል ሀገር የሰጠችኝን ግዳጅ በጽናት ተወጥቻለሁ" ያሉት ሻለቃ ባሻ ሞገስ፤ ሀገርን በውትድርና የማገልገል እድል ማግኘት ታላቅ ዕድልና ክብር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያን የመሰለች ጥንታዊት ሀገር ሉዓላዊነቷ፣ አንድነቷና ክብሯ እንዲጠበቅ አባቶቻችንም ሆኑ እኛ ዋጋ ከፍለናል፤ የአሁኑ ትውልድም ሉዓላዊነቷን አጽንቶ ለመዝለቅ ወቅቱ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዘብ መቆም አለበት ሲሉ ይመክራሉ። አሁን ያለው የሀገር መከላከያ ሠራዊት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በሰው ኃይል አቅምና ትጥቅ፣ ከሳይበር እስከ መካናይዝድ ልቆ የተደራጀ በመሆኑ ከኢትዮጵያ አልፎ ለቀጠናው ዘብ የሚሆን አስተማማኝ ኃይል መሆኑን እያየን ነው ብለዋል። "ሀገራችን የባሕር በር አልባ መሆኗ ያስቆጨኛል፤ ዕድሜ ልኬን ለሀገሬ ዘብ ብቆም ምኞቴ ነው" ያሉት ሻለቃ ባሻ ሞገስ፤ ወጣቱ ትውልድ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የተጀመረውን ተግባር በሰላማዊ መንገድ ለማሳካት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።   ሌላው የከተማዋ ነዋሪ መቶ አለቃ አበባው ገብረ እግዚአብሔር በበኩላቸው፤ «ታላቋን ሶማሊያ» ለመመስረት በሚል በጦር የሰከረው የዚያድ ባሬ መንግሥት በእብሪት ተነሳስቶ ሀገራችንን በወረረበት ወቅት በ18 ዓመታቸው የቀድሞውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት መቀላቀላቸውን ያወሳሉ። "ወላጅ አባቴ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የቀድሞ አባል ነበር" ያሉት መቶ አለቃ አበባው፤ እሳቸውና ታናሽ ወንድማቸው የአባታቸውን አሻራ በመከተል የመከላከያ ሠራዊቱን መቀላቀላቸውን ተናግረዋል። የ10ኛ፣ 19ኛ፣ እና 82ኛ ልዩ ኮማንዶ ክፍለ ጦሮች አባል በመሆን በሕክምና ሙያቸው ሠራዊቱን ለ12 ዓመታት ማገልገላቸውን ጠቁመው፤ ውትድርና ጽናትን፣ የሀገር ፍቅርን እና ከራስ በፊት ለወገን መስዋዕት መሆንን የሚጠይቅ የተከበረ ሙያ መሆኑን ገልጸዋል። ከሰራዊት አባልነት ከተገለሉም በኋላ ባካበቱት የሕክምና ሙያ በሰቆጣ ጤና ጣቢያና በተፈራ ኃይሉ ሆስፒታል ተቀጥረው ህዝባቸውን ያገለገሉ ሲሆን፣ የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ በመሆንም ሰርተዋል። "ለዘመናት ያዘንኩበት የባሕር በር ጉዳይ አሁን ላይ የትውልዱና የመንግሥት አጀንዳ ሆኖ መነሳቱ አስደስቶኛል" ያሉት መቶ አለቃ አበባው፤ ይህም የሀገራችንን የቀደመ ገናናነት የሚመልስ በመሆኑ ለስኬቱ በአንድነት መሰለፍ ይገባል ብለዋል። የአሸናፊነትና የጀግንነት ወኔ ከጥንት ጀምሮ ያለና የሚቀጥል መሆኑን አሁን ላይ የመከላከያ ሠራዊት ዘመኑን የዋጀ አደረጃጀትና የቴክኖሎጂ አቅም በማየት መገንዘብ ይቻላል ብለዋል። ወጣቱ ትውልድ ጸንታ የተከበረች ሀገሩን በአንድነትና በፍቅር ሉዓላዊነቷን ጠብቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንዳለበት መክረዋል።    
የስኬት መገለጫና የውጤት ማሳያዎች
Aug 28, 2026 647
አዲስ አበባ ነሀሴ 22/2018 (ኢዜአ) የስኬት መገለጫና የውጤት ማሳያዎች በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብና የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (Homegrown Economic Reform) እቅዶችን በመተግበር በበርካታ ዘርፎች መሠረታዊ ለውጦችን እና ስኬቶችን ማስመዝገብ ተችሏል። በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጂታል (አይሲቲ)፣ በማዕድን እና በቱሪዝም ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብታዊ አቅም ከማሳደግ ባሻገር የወደፊት ዘላቂ እድገት መሠረት ያኖሩ መሆኑን መናገር ይቻላል። በመሆኑም በአምስቱ ዋና ዋና ሴክተሮች የመጡ ውጤቶችና የተመዘገቡ ስኬቶችን በወፍ በረር እንቃኛለን። 1. በግብርና ዘርፍ የስንዴ ምርትና የውጭ ኤክስፖርት: የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መስፋፋት ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሰረት አስቀምጧል። ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የስንዴ ምርትን ወደ ውጭ ሀገር መላክ የቻለችበትን እመርታዊ ስኬትም አሳይቶናል። የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭን በመተግበር በወተት፣ በእንቁላል፣ በዶሮና የማር ምርት እንዲሁም በአትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ሩዝና ሻይ ልማትም ባለፉት አምስት አመታት እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል። አርሶ አደሩ የመሬትና የውሃ ሀብቶችን አቃፊ በሆነ መንገድ በመጠቀም በዓመት ሁለትና ሶስት ጊዜ ማምረት የሚችልበት አሰራር ተዘርግቷል። በዚህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ሁነኛ የገቢ ምንጭ የሆነበትን እድል ፈጥሯል። ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የመቻል አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል። በተለይም ደግሞ የቡና ምርታማነትና ጥራት በማደጉ ምክንያት በኤክስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማገኘት ተችሏል።   በዘርፉ በቀጣይም የግብርናውን ዘርፍ ይበልጥ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በሜካናይዜሽን በማስደገፍ ምርታማነትን የማሳደግ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። የመስኖ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት የዝናብ ጥገኝነትን ለመቀነስ መጣር እንዲሁም የግብርና ምርቶችን ጥራት በማሻሻልና በማቀነባበር ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ዋጋ ማሳደግ ተገቢ ይሆናል። 2. የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሀገራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ንቅናቄ በመፍጠር ቀደም ሲል ተቆልፈው የነበሩና በዝቅተኛ አቅምያመርቱ የነበሩ ፋብሪካዎች ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ ተደርጓል። የሀገር ውስጥ የምርት ፍላጎትን በመሸፈን ለውጭ ሀገር ምርቶች ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪም መቀነስ አስችሏል። ለሀገር ውስጥና ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ የህግና የአሰራር ሁኔታዎችን በመፍጠር በርካታ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ተችሏል። ከተገነቡት የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ፓርኮች (IAIPs) ጋር አርሶ አደሩን በማስሳሰር የግብአትና የምርት ትስስር እንዲጠናከር ተደርጓል። የአምራች ዘርፉ መስፋፋት ለብዙ ሺህ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች የሥራ እድል መፍጠር የታቸለበት ሆኗል። በቀጣይም የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በኃይል፣ በሎጂስቲክስና በግብአት አቅርቦት ሙሉ በሙሉ በመደገፍ ኤክስፖርትን ማሳደግ። የአምራች ኢንዱስትሪዎች 80% እና ከዚያ በላይ የሀገር ውስጥ ጥሬ ዕቃዎችን እንዲጠቀሙ ማበረታታት፣ በህዝብና በግል አጋርነት (PPP) አማካኝነት በትልልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ላይ የግሉን ዘርፍ አሳትፎ ማስፋፋት ትኩረት የሚደረግበት ይሆናል።   3. የዲጂታል (አይሲቲ) ዘርፍ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ስልት ስኬቶችን በማስቀጠል ወደ "ዲጂታል 2030" እቅድ መሸጋገር ተችሏል። በ"መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በሌሎች ፖርታሎች አማካኝነት ህዝባዊ አገልግሎቶችን በበይነ-መረብ (Online) የመስጠት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የዜጎችን መረጃ ማዕከላዊ የሚያደርግና ለፋይናንስ እንዲሁም ለሌሎች አገልግሎቶች መሠረት የሆነውን የፋይዳ መታወቂያ ፕሮጀክት በላቀ መልኩ ማሳካት ተችሏል። የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን የኮደር ስልጠናም የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ ታላቅ ሀገራዊ የስልጠና መርሃ ግብር ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።የዲጂታል አገልግሎቶች መዘርጋታቸው የፊት ለፊት ግንኙነትን በመቀነስ ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን በመከላከል የኢንቨስትመንት ምህዳሩን አሳልጧል። የቴሌኮም ዘርፍ ውድድር: የቴሌኮም ዘርፉን ክፍት ማድረግን ተከትሎ የኢንተርኔትና የኔትወርክ ተዳራሽነትንና ጥራትን በየገጠሩ የማስፋት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቶችን እና የባንክ አገልግሎቶችን ይበልጥ ዘመናዊና የተቀናጁ ማድረግም አስፈላጊ ይሆናል። የሀገሪቱን የዲጂታል መሠረተ ልማት ከሳይበር ጥቃቶች የመጠበቅ አቅምን ማጠናከር። 4. የማዕድን ዘርፍ በዘርፉ ይስተዋል የነበረውን ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ በመግታት ህጋዊ አሰራርና ቁጥጥር እንዲሰፍን ተደርጓል። የህግና መመሪያዎች ማሻሻያ በማድረግ የማዕድን ዘርፉን ለውጭና ሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ማራኪ የሚያደርጉ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ተደርገዋል። የወርቅ፣ የከሰል ድንጋይ፣ የሲሚንቶ ግብአቶችና የከበሩ ድንጋዮች ምርትን በማሳደግ ዘርፉ የሀገሪቱ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ እንዲሆን ተሰርቷል። በተለይም የከሰል ድንጋይ ምርትን በሀገር ውስጥ አምርቶ በመተካት ለፋብሪካዎች ግብአት ማቅረብ ተችሏል። 5. የቱሪዝም ዘርፍ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር)አነሳሽነት የተጀመሩት "ገበታ ለሸገር"፣ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች በመላ ሀገሪቱ በርካታ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን መገንባት ተችሏል። በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች የተከናወኑ የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበትና ለኑሮ ምቹነት ከመጨመራቸው ባሻገር ለከተማ ቱሪዝም ትልቅ እድል ፈጥረዋል። አዲስ አበባ በርካታ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችንና ኮንፈረንሶችን ባካሄደችበት የዲፕሎማሲና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷን አጠናክራለች።   የሀገሪቱን ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች የመጠበቅ፣ የማደስና ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራዎች በስፋት ተከናውነዋል። በድምሩ ባለፉት አምስት ዓመታት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጂታል፣ በማዕድን እና በቱሪዝም ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች ሀገሪቷን ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ምዕራፍ ማሸጋገር አስችለዋል። በመሆኑም እነዚህን ስኬቶች አጠናክሮ ለማስቀጠል የታቀዱትን የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች በተቀናጀ መልኩ መተግበር፣ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ እና የግሉን ዘርፍ አሳታፊነት ማሳደግ በቀጣይ አዲስ የሚመሰረተው መንግስት ዋነኛ የቤት ስራ ይሆናል።  
ትንታኔዎች
የዲጂታል አብዮት ለነገዋ ኢትዮጵያ
Sep 9, 2026 295
በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ የዛሬን ፈታኝ ሁኔታዎች ከመቅረፍ ባለፈ፣ ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር በፍጥነት እያሸጋገራት ይገኛል። የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታዎች እና የተቋማት ማጠናከሪያ ስራዎች ለዚሁ አገራዊ የነገ ትራንስፎርሜሽን በምሳሌነት የሚጠቀሱ ዋና ዋና እርምጃዎች ናቸው። መንግስት የዲጂታል ዘርፉን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሶሶ በማድረግ የነደፈውን "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ስትራቴጂ በስኬት ማጠናቀቁ፣ 2030 ዲጂታል ስትራቴጂን መጀመሩ ሀገሪቱን በቴክኖሎጂው ዘርፍ ወደ አዲስ የወደፊት ምዕራፍ እንድትገባ ያስቻለ መሰረታዊ ለውጥ አምጥቷል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ፣ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም መዘመን ለኢንተርኔት ተደራሽነት መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። በተለይም የ5G ቴክኖሎጂ አገልግሎት በስፋት መጀመሩ ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ በቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትና በመሰረተ ልማት ዝግጁነት ቀዳሚ ያደረጋት ሲሆን፣ ይህም ለነገው ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እና ለቀጣይ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቱ መዘመን በፋይናንስ ዘርፉ ላይ አብዮታዊ ለውጥ በማምጣት የነገዋን ስማርት ኢኮኖሚ መደላደል ጥሏል። እንደ ቴሌብር ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ ለአካታች ዲጂታል ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም ሆነዋል። ይህ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ምህዳር መስፋፋት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የዲጂታል ክፍያዎችን እንዲቀበሉና የፋይናንስ ተደራሽነታቸው እንዲያድግ ያስቻለ ሲሆን፣ መደበኛ ያልሆነውን የግብይት ስርዓት ወደ ዘመናዊና ግልጽ የነገ ዲጂታል ስርዓት የመቀየር ሂደቱን አፋጥኖታል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የኢትዮጵያ ሰውሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም የሀገሪቱን ታላቅ የነገ ራዕይ ለዓለም አሳይቷል። ኢንስቲትዩቱ በጤናው ዘርፍ የካንሰርና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ የሚያውቁ የኤአይ ውጤቶችን በማበልጸግ ህይወትን የማዳን ስራ እያከናወነ ይገኛል። በተመሳሳይ በግብርናው ዘርፍ የአፈር ለምነትንና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም ለነገዋ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥና ለምርታማነት ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ የለውጡ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል አለም ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱ በማድረግ ለነገው ትውልድ የባህል እና የእውቀት መተላለፊያ ምቹ መንገድ ፈጥሯል። ከዚሁ ጎን ለጎን የ"ፋይዳ" (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት የዜጎችን መረጃ በማደራጀት ለነገው ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ አስተማማኝ የመረጃ መሰረት ጥሏል። ይህም ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ቀልጣፋ አሰራርን ፈጥሯል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የነገዋን አሰራር ዛሬ ማሳያ ሲሆን፣ የሳይንስ ሙዚየም ደግሞ የነገዎቹን ፈጣሪዎች አቅም የሚያበለጽግ ማዕከል ሆኗል። በተጨማሪም በዲጂታል ክህሎት ግንባታ ረገድ ለወጣቶችና ለባለሙያዎች የሚሰጡ የስልጠና ፕሮግራሞች በስፋት እየተካሄዱ ይገኛሉ። ይህም ኢትዮጵያ በነገው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መድረክ ብቁ እና ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ኃይል እንድታፈራ ዘላቂ መሰረት እየጣለ ነው።
ነገን በብልሃት ማነጽ - የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ
Sep 9, 2026 229
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የጀመረችውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አጠናክራ ለመቀጠል እና ከጊዜው ፈጣን የቴክኖሎጂ እድገት ጋር ለመራመድ “የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂን በይፋ አድርጋለች። ታኅሣሥ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው ይህ ታላቅ አገራዊ ዕቅድ፤ ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዓለም ከተመልካችነት ይልቅ ተሳታፊና መሪ የምትሆንበትን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው። ይህ አዲስ ስትራቴጂ ከቁጥሮች እና ከኢኮኖሚያዊ ስኬቶች ባሻገር፣ ዛሬን ከመቅረጽ ባለፈ ነገን ከመገንባት እና ለቀጣይ ትውልድ አሻራ ከማስቀመጥ አንጻር ሰፊና ጥልቅ ፋይዳ ያለው ሀገራዊ ትልም ነው። በዲጂታል ዘመን የመረጃ ሉዓላዊነት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው ። በዚህ ዘርፍ የሚያጋጥም ጥገኝነት የሃገር ደህንነት ላይም የራሱን አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳረፉ አይቀርም። ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዚህ ዙሪያ መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ ነው ማለታቸው ይታወሳል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነውም ብለዋል። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ከወረቀት ባለፈ በህዝብና በሀገር ላይ የሚኖረው ተጨባጭ ማሳያ በአጭር ጊዜ ውስጥ መሬት የረገጠ እውነታ ነው። ለአብነት ያህል፣ በዓለም ሁለተኛውና ለአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ግንባታ መጀመሩ እና ከዩኤንዲፒ ጋር በመተባበር የተመረቀው 'AI UniPod' ማዕከል ለወጣቶች የተፈጠረ ትልቅ የቴክኖሎጂ መሠረት ነው። ተቋማቱ ከሀገር ውስጥ አልፎ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል በማመቻቸት ላይ መሆናቸው፣ ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የፈጠራ ማዕከል ሆና እንድትቀጥል የሚያስችላት የትውልድ አሻራ ነው። የሞባይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር 128 ሚሊዮን ለማድረስ እንዲሁም የ5G ኔትወርክ ተደራሽነትን ሙሉ በሙሉ እውን ለማድረግ የተነደፈው ዕቅድ፣ በከተማና በገጠር መካከል የነበረውን የዲጂታል ክፍተት በማጥበብ የመረጃ እኩልነትን የሚያረጋግጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው። እንደ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከመሳሰሉ መሠረተ ልማቶች ጋር ተቀናጅቶ የሚሰራው ይህ እቅድ፣ የዜጎችን ተደራሽነት በማስፋት እኩል እድል የሚፈጥር አሰራርን ይዘረጋል። ይህ የዲጂታል መረብ መስፋፋት የዜጎችን ኑሮ በጥራት ከማሻሻል ባለፈ አገልግሎቶች በፍጥነት እንዲቀላጠፉ ትልቅ አቅም ይፈጥራል። የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ ለማድረግ የሚከናወነው አሰራር ግልጽነትን በማስፈን በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመንን ያጎለብታል። ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የዛሬን ስኬት ብቻ ሳይሆን የወደፊቱን ትውልድ አዕምሮ በዕውቀትና በፈጠራ ብርሃን በመቅረጽ የሀገርን የሰው ሀብት በዘላቂነት የሚያለማ የዕድገት ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው ካነጣጠረባቸው ቁልፍ ነጥቦች መካከል ተደራሽነትን ማስፋት፣ እኩል እድል መፍጠር እና በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ይገኙበታል። ግልጽነት የሰፈነበት፣ ከወረቀትና ከቢሮክራሲ የጸዳ አሰራር መዘርጋቱ ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ላይ ያላቸውን እምነት ያጠናክራል። ይህ ደግሞ ማህበራዊ መተሳሰርን አጠናክሮ ለአንድነትና ለጋራ ብልጽግና መሰረት የሚጥል ትውልድ ተሻጋሪ ስራም ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ሥራ ዕድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት የወጣቶችን ፈጠራ ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም መቀየር ያስችላል። ወጣቱ በዲጂታል ንግድ፣ በሶፍትዌር ልማት እና በዲጂታል አገልግሎቶች ላይ ተሰማርቶ በራሱ ጥረት እያደገ ሲሄድ፣ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ መሠረት የጸና ይሆናል። የዲጂታል ኢኮኖሚ እያደገ ሲሄድ የሳይበር ደህንነት እና የመረጃ ጥበቃ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የሳይበር ደህንነት መሠረተ ልማቶችን ማጠናከሩን እንደ ዋና ዕቅድ ይዞ መንቀሳቀሱ ዜጎችና ተቋማት በአስተማማኝ ዲጂታል ምህዳር ውስጥ እንዲኖሩ ያስችላል። ቴክኖሎጂ የሉዓላዊነት ሌላኛው መገለጫ በመሆኑ፣ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማትን ማስፋት ወሳኝ ነው። መረጃዎች በውጭ አካላት ቁጥጥር ስር ሲሆኑ የሀገር ደህንነት አደጋ ላይ ይወድቃል። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የመረጃ ደህንነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የሚያስችል አቅም በመፍጠር ለነገው ትውልድ የባለቤትነት ስሜት ያጎናጸፋል። ወጣቶች በሮቦቲክስ፣ በዳታ ሳይንስ እና በሶፍትዌር ልማት ላይ ሲሰማሩ፣ ችግሮችን በፈጠራ ሃሳብ የሚፈቱ አዳዲስ ጅምሮች ይፈጠራሉ። ይህም የወጣቱን የእውቀት አቅምና ክህሎት ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ ውጤት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ ራሱን የቻለ የኢኮኖሚ መሠረት ይጥላል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ስኬት ከተቀናጀ የመደመር እሳቤ ጋር የሚተሳሰር ነው። ነገን የተረጋጋ ሰላምና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና የምናረጋግጥበት ሁነኛ መንገድም ጭምር ።
የስንዴ አብዮት፦ የኢትዮጵያ ማንሰራራት አብነት
Sep 6, 2026 602
ኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ107 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ነው። ይህንን ፍላጎት ለማሟላት ለዓመታት ከ700 ሚሊዮን ዶላር እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ውድ የውጭ ምንዛሬ ለስንዴ ግዢ ስታወጣ ቆይታለች። ከዚህ ቀደም ሀገሪቱ ከዓመታዊ ፍላጎቷ መሸፈን የምትችለው ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ብቻ ሲሆን፣ ቀሪውን በውጭ ግዢ ትሸፍን ነበር። በተለይም የዩክሬንና የሩሲያ ጦርነት በዓለም አቀፍ ደረጃ 30 በመቶ የሚሆነውን የስንዴ አቅርቦት በማወኩ ኢትዮጵያ ከባድ የአቅርቦት ፈተና ውስጥ እንድትገባ አድርጓት ነበር። ይህንን የረጅም ጊዜ ተግዳሮት በዘላቂነት ለመቅረፍ መንግሥት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በስፋት በመተግበር፣አሲዳማ መሬቶችን በኖራ በማከም እና ረግረጋማ ቦታዎችን በቴክኖሎጂ በማድረቅ ታሪካዊ ለውጥ ለማምጣት እርምጃዎችን ወስዷል። በኩታ ገጠም እርሻና በዘመናዊ ማሽነሪዎች አጠቃቀም የታጀበው ይህ የልማት አብዮት ፍሬ አፍርቶ፣ ኢትዮጵያ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ከውጭ የምታስገባውን የንግድ ስንዴ ሙሉ በሙሉ አቁማለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስንዴ ልማት የተመዘገበው ስኬት ከውጭ ማስገባትን ማቆም ላይ ብቻ ሳይወሰን፣ ሀገሪቱ ወደ ውጭ መላክ (ኤክስፖርት ማድረግ) የሚያስችል አቅም እንዳላት ያሳየ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም መሠረት የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን በይፋ የስንዴ ኤክስፖርት የተጀመረ ሲሆን፣ ለዚህ ስኬታማነት የተለያዩ ክልሎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚና የኤክስፖርት ኮሚቴ ሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ፍጆታዋን ሸፍና 32 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም እንዳላት አረጋግጦ፣የ2.9 ሚሊዮን ኩንታል የውል ስምምነቶች ከረድኤትና ከሀገር ውስጥ ድርጅቶች ጋር ተፈራርሟል። ከሀገር ውስጥ አቅርቦት ባሻገር ኢትዮጵያ በ2015 ዓ.ም ለኬንያ ስንዴ ለመላክ ስምምነት የፈረመች ሲሆን፣ ጅቡቲም ከኢትዮጵያ ስንዴ መግዛት እንደምትፈልግ ገልጻ ከኢትዮጵያ የስንዴ ልማት ብዙ ተሞክሮ እንደምትወስድ አመላክታለች። የአፍሪካ ልማት ባንክ ስንዴ ከውጭ እንደማታስገባ እና ምርቷን ለጎረቤት ሀገራት ማስተላለፍ መጀመሯን በማድነቅ ለአህጉሪቱ እንደ ትልቅ የዕድገት ተሞክሮ አቅርቧል። የአሜሪካ የውጭ ግብርና ቢሮ ሪፖርቶችም በኢትዮጵያ የስንዴ ምርት ዘርፍ ትልቅ እመርታ እያሳየ መምጣቱን ጠቅሰው፣መንግሥት የመስኖ ልማትና የግብርና ኤክስቴንሽን ድጋፍ በማጠናከሩ ሀገሪቱ ከፍተኛ ምርት ማምረቷን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ምርት ከ290 እስከ 340 ሚሊዮን ኩንታል (ከ29 እስከ 34 ሚሊዮን ቶን) በላይ መድረሱ ኢትዮጵያን በአፍሪካ አህጉር ቀዳሚ የስንዴ አምራች ሀገር አድርጓታል። የስንዴ ልማቱ አርሶ አደሩን ከቀድሞው ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ አላቆ፣ በኩታ ገጠም እርሻና በሜካናይዜሽን ታግዞ ወደ ሰፋፊ የንግድ ምርት እንዲገባ አስችሏል። የተሻሻሉ የስንዴ የሰብል ዝርያዎች መለቀቃቸው ለዚህ ውጤት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ የምርት አቅርቦት ሰንሰለቱን ማዘመን በቀጣይነት በትኩረት እየተሠራበት ይገኛል። በምርት አቅም እና በኩታ ገጠም እርሻ የተመዘገቡት እነዚህ ሰፊ ስኬቶች፣ ሀገሪቱ በኢኮኖሚ አቅም እያደረገችው ያለውን ሁለገብ ማንሰራራት በግልጽ የሚያሳዩ አብነቶች ናቸው። ይህ ትልቅ ለውጥ ኢትዮጵያ ከድህነትና ከዕርዳታ ጥገኝነት ወጥታ የምግብ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ ለሌሎች አፍሪካ ሀገራትም ተስፋ የሚሰጥ አህጉራዊ አርዓያ መሆን መቻሏን አስመስክሯል። ይህ የምርት እመርታ በግብርናው ብቻ ሳይሆን፣ አጠቃላይ የሀገሪቱን ማንሰራራት የሚያረጋግጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው። ለዘመናት በውጭ ዕርዳታና በለጋሾች ላይ ተወሰና የነበረችው ኢትዮጵያ፣ዛሬ በራሷ አቅም በመሥራት አህጉራዊ አርዓያ መሆን መቻሏ ትልቅ ስኬት ነው። የኢኮኖሚ ነፃነት እና የሉዓላዊነት ማዕቀፍን በማረጋገጥ ረገድም የስንዴ አብዮቱ የሀገርን አቅም የሚያሳይ ተምሳሌት ሆኗል። በመሆኑም በስንዴ ልማት የተገኘው ይህ ድል የግብርና ዘርፍ ስኬት ብቻ አይደለም፤ ኢትዮጵያውያን በቁርጠኝነትና በትጋት ከሠሩ ሀገርን ማሻገር እንደሚችሉ በተግባር ያረጋገጡበት ታላቅ የሀገር የማንሰራራት ማሳያ ነው።
የቡና ወጪ ንግድ እድገት - የኢትዮጵያ እመርታ አንዱ ማሳያ
Sep 5, 2026 456
ገና ወደ ውስጥ ሲገቡ ለምለም ቄጠማ በተጎዘጎዘበት ቤት እና ትኩስ በተቆላ ቡና ከደማቅ ፈገግታ ጋር አቀባበል ታደርጋለች። የቡናው ሽታ ደግሞ ልዩ መዐዛ አለው። አለምነሽ ሀብቱ ወደ ከተማ ከገባች በኋላ ድሮም የምትወደውን ቡና የሰርክ ስራዋ የእለት መተዳደሪያዋ አድርጋዋለች። ቡና ትወዳለች የአዘገጃጀት ድምቀቷንም ሌሎች ይወዱላታል። እሷ የምታዘጋጀውን የጀበና ቡና ለመጠጣት የመጣ ደንበኛዋ አትርፎ እንደወጣ እንዲሰማው የማድረግ ተሰጥኦ አላት። ቡና ትወዳለች ትጠጣለች ታጠጣለች ። እንደሷ ሁሉ ቡና ለኛ ለኢትዮጵያውያን አብሮን የሚውል፣ የሚያመሽ በብዙዎቻችን ቤት በቋሚነት የማይጠፋ ማህበራዊ መገናኛችን መመካከሪያችንም ጭምር ነው። በቡና ምርት በርካታ መሬትን ሸፍና ብዙ አርሶ አደሮችን እያሳተፈች የወጪ ንግዷን ለማሳደግ የምትጥረው ኢትዮጵያ ደግሞ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የምታገኝበት ዋንኛ የግብርና ኢኮኖሚው የጀርባ አጥንትም ነው። ባለፉት ዓመታት የቡና ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ድርሻም እያሳደገ መምጣቱን የተለያዩ መረጃዎች እያሳዩ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄ ማብራሪያ ሲሰጡ ለቡና ልማት የተሰጠው ትኩረት ኢትዮጵያን በአለም ሶስተኛዋ ቡና ላኪ ሀገር እንድትሆን ማስቻሉን ማንሳታቸው ይታወሳል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ከቡና ወጪ ንግድ የተገኘው ከ3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ወደ ውጭ ከላከቻቸው ምርቶች ከፍተኛው እንደነበረም አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከብራዚልና ከኮሎምቢያ በመቀጠል በዓለም 3ኛዋ ትልቋ የቡና ላኪ ሀገር መሆኗን እና በአፍሪካም ቀዳሚ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የሀገር ውስጥ የቡና ፍጆታ ከመቻል አልፈን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የመጣው ለውጥ የሀገራዊ የሪፎርሙ ስኬት መገለጫ ነው ማለታቸውም ይታወሳል። ይህ የአንድ ዓመት ምርት እንግዲህ ኢትዮጵያ ባለፉት 17 አመታት ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ካገኘችው 3 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ጠቅላላ ገቢ ጋር ሲነጻጸር አስደማሚ ስኬት መሆኑ አያጠራጥርም። አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለቡና ኤክስፖርት እድገት ስኬት አስተዋጽኦ ማበርከቱን በወቅቱ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቡናን ካልተከልን ፤ ካልተንከባከብን ፤ካልለቀምን፤ ካላጠብን፤ካላሸግንና ካላጓጓዝን ይህ ውጤት ሊመጣ አይችልም ብለውም ነበር። ኢትዮጵያ የአረቢካ ቡና መገኛ እንደመሆኗ የምርቱን እድገትና ዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ተፈላጊነቱን ለማሳደግ እየተከናወኑ ባሉ ተከታታይ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል። ባለፉት ተከታታይ ዓመታት የተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በሌሎች ኢኮኖሚያዊ፣ አካባቢያዊና የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳራዊ ግዙፍ አበርክቶው እንዳለ ሆኖ በቡና ምርት እድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ለዚህ ማሳያው ደግሞ መርሃ-ግብሩ ሲጀመር በ2011 ዓ.ም. ስድስት መቶ ሺህ ችግኝ የተተከለ ሲሆን ዓመታዊ ምርቱም 5 መቶ ሺህ ሜትሪክ ቶን ነበረ። በወቅቱ የተገኘው የውጭ ምንዛሪም 738 ሚሊዮን ዶላር ነበር። ይሄ ትኩረት በመቀጠሉም የቡና ችግኝ የመትከሉ ስራ አድጎ በ2017 ዓ.ም. ላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን በዛው ዓመት 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ተችሏል። ከላይ እንደተገለጸው የ2018 የቡና ወጪ ንግድ ገቢ 3 ነጥብ 1 መድረሱ ለዘርፉ የተሰጠውን ትኩረት እና የተመዘገበውን እመርታ የሚያሳይ ነው። ለዓመታት በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የቆየው የቡና ወጪ ንግድ ገቢ በአጭር ጊዜ መለወጥ እና ኢትዮጵያ ወደ ተለያዩ ሃገራት ከምትልካቸው የግብርና ምርቶች ከፍተኛውን ድርሻ ይዞ መቀጠሉ ለዘርፉ ለተሰጠው ትኩረት እና ለተገኘው ውጤት አንዱ መገለጫም ነው። የኢትዮጵያ ቡና በዓለም ገበያ ላይ ተፈላጊነቱ በየጊዜው እየጨመረም ይገኛል። ጀርመን፣ አሜሪካ፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ጃፓን፣ ቤልጂየም እና ደቡብ ኮሪያ ከቀዳሚዎቹ የኢትዮጵያ ቡና ገዢዎች መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን በቻይና እና በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የቡና ፍጆታና የመጠጣት ባህል በፍጥነት ማደጉ ለኢትዮጵያ አዳዲስ የገበያ እድሎችን ፈጥሯል። ይህ የኢትዮጵያ የእመርታ ጉዞ በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል ብልጽግናዋንም የምታረጋግጥ የዳበረ ኢኮኖሚ ያላትና የበለጠ ጠንካራ ሀገርነቷን የምታስቀጥልበት አዲስ ምዕራፍም ነው።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 13040
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 22331
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 15361
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 21103
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 106466
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 80528
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 58858
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 56464
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 40242
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 40158
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 39611
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 38092
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 106466
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 80528
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 58858
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 56464
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በጎነት የሰብዓዊ ክብር መሠረት፤ የመደመር መንግሥት የሰው ተኮር ልማት የተስፋ አድማስ
Sep 11, 2026 376
በጎነት ከኢትዮጵያውያን የዕለት ተዕለት ኑሮና እንቅስቃሴ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ፣ ከራስ ቀንሶ ለሌሎች መድረስ የሚገለጽበት ከፍ ያለ ሰብዓዊ እሴት ነው። በጎነት የግለሰብን ችግር ብቻ የሚያቃልል ተግባር አይደለም። የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክፍተቶችን በመሙላት አብሮነትን፣ መተሳሰብንና የጋራ ኃላፊነትን የሚያጠናክር የማህበራዊ ኃላፊነት ውልም ነው። ''ሃምሳ ሎሚ ለሃምሳ ሰው ጌጡ፤ ለአንድ ሰው ሸክሙ” እንዲል የሀገር ብሂል ሰዎች በአንድነት ቆመው ለአንድ መልካም ዓላማ ከተባበሩ ለመፍታት የማይቻል ችግር እንደሌለ በተግባር የሚያሳዩ ብዙ አብነቶች አሉ። በተለይም በሰው ተኮር ልማትና በበጎ ፈቃድ የሚከናወኑ የቤት ግንባታና እድሳት ሥራዎች ችግርን ከመቅረፍ ባለፈ የሰዎችን ሰብዓዊ ክብር የሚመልሱ የተስፋ ምንጭ ተግባራት ሆነዋል።   ባለፉት ዓመታት በሀገር አቀፍም ሆነ በአዲስ አበባ በበጋና ክረምት ሰው ተኮር የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሮች በርካታ ዜጎችን ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉስቁልና ወደ ልዕልና እንዲሸጋገሩ አስችሏል። ከእነዚህ የሰው ተኮር ተግባራት ተጠቃሚ ከሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች መካከል በመኖሪያ ቤት ችግር ምክንያት ኑሯቸው በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የነበሩ ነዋሪዎች ይገኙበታል። ቤት ለአንድ ሰው የመኖሪያ ቦታ ብቻ አይደለም። ይልቁንም የዜጎችን የደህንነት፣ የክብር፣ የመረጋጋትና ዘላቂ የተስፋ ወጋገን የሚያቆራኝ መሰረታዊ ጉዳይ ነው። ስለዚህ ለአንድ ቤተሰብ የሚገነባ ወይም የሚታደስ ቤት ከግንባታ ዕቃና ከግድግዳ በላይ ትርጉም አለው፤ የተሰበረ ተስፋን ይጠግናል፣ የተረሳ ክብርን ይመልሳል፣ ለነገም አዲስ እድል ይከፍታል። በአዲስ አበባ በበጎ ፈቃደኞች፣ በባለሀብቶችና በመንግሥት የጋራ ጥረት ቤት ተገንብቶላቸው እፎይታን ያገኙ ነፍሶችም በርካቶች ናቸው።   ወይዘሮ መስከረም ሰለሞን እንደሚሉት፤ ከዓመታት በፊት ከሁለት ልጆቻቸው ጋር ፒያሳ አካባቢ ለሰው ልጅ ክብርን በማይመጥን ጎስቋላ ቤት ውስጥ ሕይወትን ይመሩ ነበር። በተለይም ክረምት በመጣ ቁጥር የጎርፍና የዝናብ ፍሳሽ አደጋ በከፍተኛ ጭንቀት እንዲያሳልፉ ያስገድዳቸው እንደነበር አስታውሰዋል። በሳር ቤት አካባቢ በተሰራላቸው ዘመናዊ የመኖሪያ መንደር የተሰጣቸው የመኖሪያ ቤት አዲስ የሕይወት ተስፋን እንዳጎናጸፋቸው አስረድተዋል። ይህንም ለመኖር ከማይመች ቦታ ወጥቼ ወደ አማረ ቤት በመግባቴ እንደገና የመወለድ ያህል ታላቅ ደስታ ተሰምቶኛል ሲሉ ገልጸዋል። እንደ ወይዘሮ መስከረም ታሪክ ሁሉ የሌሎች ነዋሪዎች የቤት ግንባታና ዕድሳት ሥራዎች ተሞክሮ የሚያሳየው የቁሳዊ እፎይታ ብቻ ሳይሆኑ ሰብዓዊ ክብርን የሚያጎናጽፉ የተስፋ ውጤቶች መሆናቸውን ነው።   በአንድ ወቅት ከፎቅ ላይ ባጋጠማት የመውደቅ አደጋ ሳቢያ የአካል ጉዳት ያጋጠማት ታሪክ ሙሉጌታ፤ በአዲስ አበባ በኪራይና በመንግሥት ቤት ከቤተሰቧ ጋር ሕይወትን ስትገፋ እንደነበር ገልጻለች። የአካል ጉዳተኛ ከሆነች በኋላ ቀደም ሲል ትኖርበት የነበረው ቤትና አካባቢ ከቦታ ቦታ እንደልብ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ እንደነበር በማስታወስ፤ ከቤተሰቧ ጋር ይኖሩበት ከነበረው ባምቢስ አካባቢ ወደ ሳር ቤት አካባቢ የመኖሪያ ቤት ማግኘቷ በሕይወት ዘመን ያገኘሁት ትልቅ የተስፋ ስጦታዬ ነው ብላለች። ቤቱ እንደልብ መንቀሳቀስ የሚያስችል፣ መሠረታዊ የመኖሪያነት መስፈርቶች የተሟላላት መሆኑ ሕይወቴን በትልቅ እፎይታ እንድመራ አስችሎኛል ስትል ተናግራለች። በሰው ተኮር ፕሮጀክት የሚገነቡ ቤቶች የሚያመጡት ለውጥ ለአካል ጉዳተኞች ብቻ የሚወሰን አይደለም። በቤት ውስጥ ልጆች፣ አረጋውያን፣ የሀገር ባለውለታዎችና መላ ቤተሰብ እንዲሁም የተሻለ ኑሮን ለመፍጠር የሚታገሉ እናቶችና አባቶችም የዚህ ተግባር ተጠቃሚዎች ናቸው። በዚህም በጎነት የአንድን ሰው ዛሬ ከማሻሻል ባለፈ የአንድ ቤተሰብን ነገ የሚቀርጽ ኃይል መሆኑን ያሳያል።   ወይዘሮ ጽጌሬዳ ጎበና ፤ ለረጅም ዓመታት ፒያሳ አካባቢ ለመኖር ምቹ ባልሆነ ቤትና ሰፈር ከአንድ ልጃቸው ጋር ይኖሩ ነበር። በፒያሳ አካባቢ የሕይወት ቆይታ ዘመናቸውም ልዩ ድጋፍ የምትሻው ልጃቸው እንደልቧ መንቀሳቀስ የማትችልበትን በርካታ የሰቆቃ ጊዜያት እንዳሳለፈች አስታውሰዋል። በዚህ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ እያሉ በሳር ቤት አካባቢ አዲስ ቤት ማግኘታቸው እንደገና የመወለድ ያህል ትልቅ እፎይታን እንደቸራቸው ገልጸዋል። የተሰጣቸው ቤት ለልጃቸው እንቅስቃሴ ምቹ ከመሆኑ ባለፈ ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤን እንዲከተሉ ያስቻለ ታላቅ የሕይወት ብስራት መሆኑን ገልጸዋል። እነዚህ ታሪኮች የሚያስረዱት አንድ ቤት ሲታደስ ግድግዳና ጣሪያ ብቻ አለመሆኑን ነው። ከቤቱ ጋር የነዋሪው ተስፋ፣ የቤተሰቡ መረጋጋትና የሰው ልጅ ክብርም አብሮ ይታደሳል። በዚህም በጎነት የችግር መፍቻ ብቻ ሳይሆን ከጊዜ ጊዜ የተስፋ ማስፈንጠሪያና ሰብዓዊ ክብር ማጎናጸፊያ ተግባር እየሆነ መጥቷል።   በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቤታቸው ከታደሰላቸው መካከል ታየሁ መኮንን እንደሚሉት፤ ቀደም ሲል ይኖሩበት የነበረው ቤት 'ቤት ነው ለማለት እንኳን አያስደፍርም' ነበር። ዛሬ ግን ታሪካቸው ተቀይሯል። በበጎ ፈቃደኞች አማካኝነት የመኖሪያ ቤት ችግራቸው ተቀርፎ፣ 'ቤቴ በመታደሱ ያለ ሀሳብ ጎኔን ማሳረፍ ችያለሁ' ሲሉም ወይዘሮ ታየሁ ገልጸዋል። ይህ አንድ ነዋሪ ያገኘው የቤት ለውጥ ብቻ አይደለም። ከዓመታት የጭንቀት ኑሮ ወደ መረጋጋት የተሸጋገረ ሕይወት ነው። ከስጋት ወደ እፎይታ፣ ከተስፋ መቁረጥ ወደ ተስፋ የተደረገ ጉዞ ነው። ለበርካታ ዓመታት በማይመች ቤት ኑሮ ሲገፉ እንደቆዩ የገለጹት ወይዘሮ ዘውዲቱ ገብረማርያም ደግሞ፤ አሁን ላይ ቤታቸው በመታደሱ ደስ ብሏቸው የሚኖሩበትን ዕድል እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።   በሰው ተኮር የልማት መርሃ ግብር አቅመ ደካማ ወገኖችን ለመደገፍ የሚከናወኑ ተግባራትም የበርካቶችን ተስፋ የሚያለመልም አስደናቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። እነዚህ የነዋሪዎች ምስክርነቶች በጎነት በተግባር ሲገለጽ የሰውን ክብር እንደሚያጎናጽፍ፣ የተሰበረ ተስፋን እንደሚያድስና ለነገ የሚያስብ ሕይወትን እንደሚፈጥር ያረጋግጣሉ። በተለይም እናቶች፣ አረጋውያን፣ አቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎች የሚያገኙት ድጋፍ በቁሳዊ እርዳታ ብቻ የሚመዘን ሳይሆን 'እናንተም የዚህ ሀገር ክብር ናችሁ' የሚልን ሰብዓዊ መልዕክትን ያስተላልፋል። በዚህ ረገድ የመደመር መንግሥት ሰው ተኮር ልማትን እንደ የልማት ፖሊሲ አቅጣጫ በመያዝ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክፍተቶች በመሙላት ተስፋን የሚያለመልሙ ተግባራትን እያጠናከረ ይገኛል። የቤት ግንባታና ዕድሳት፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችና ሌሎች ሰው ተኮር መርሃ ግብሮችም ይህንኑ አቅጣጫ በተግባር ከሚያሳዩ ተጨባጭ ለውጦች መካከል ይጠቀሳሉ። አስተያየት ሰጪዎቹ ዛሬ ላይ ውብና ጽዱ በሆነ ቤት የሚኖሩበት ዕድል የተፈጠረው መንግሥት፣ ባለሀብቶችና ሌሎች በጎ ፈቃደኞች ባከናወኑት መልካም ተግባር በመሆኑ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በአዲስ አበባ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት አረጋውያንን፣ አቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎችን አመቺ መጠለያ እንዲያገኙ ለማድረግ የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በእርግጥም የበጎነት ዋጋው በሚሰጠው የቁሳቁስ መጠን ብቻ አይለካም። በሰው ልብ ውስጥ በሚፈጥረው ተስፋና በሕይወት ላይ በሚያመጣው ለውጥ ይመዘናል። የተሰራው ቤት ለአንዲት እናት የእፎይታ ምንጭ፣ ለአንድ አረጋዊ የክብር መገኛ፣ ለአካል ጉዳተኛ ደግሞ በራስ መተማመንና ነፃነት መገለጫ ይሆናሉ።   ይህም ሰው ተኮር ልማት ማለት ትልልቅ ፕሮጀክቶችን መገንባት ብቻ ሳይሆን፣ የአንድ ዜጋን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል፣ የአንድ ቤተሰብን ተስፋ ማደስና የአንድን ሰው ክብር ማስመለስ ጭምር መሆኑን ያሳያል። በጎነት ከአንድ ሰው ወደ ሌላው የሚሸጋገር ቀላል የመልካም ተግባር መገለጫ ቢመስልም በጋራ ሲተገበር ማኅበረሰብን የመለወጥ ታላቅ ኃይል አለው። የእነዚህ ነዋሪዎች ታሪክም ይህንኑ ያረጋግጣል። ከተስፋ መቁረጥ ወደ ተስፋ፣ ከስጋት ወደ እፎይታ፣ ከአስቸጋሪ ኑሮ ወደ የተሻለ ኑሮ የተሸጋገሩ ሕይወቶችን ያሳያል። ስለሆነም በጎነትን እንደ የአንድ ጊዜ ዘመቻ ሳይሆን እንደ የማኅበረሰብ የጋራ እሴት ማጠናከር፣ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን መደገፍና ሰው ተኮር ልማትን ማስቀጠል የጋራ ኃላፊነት ነው። ዛሬ የተሰራ ቤት ከግድግዳ በላይ ነው። የነገ ተስፋ መሰረት ነው። ዛሬ የተዘረጋ የበጎነት እጅም ከአንድ ሰው የሚተርፍ ለብዙዎች የሚደርስ የሰብዓዊነት ብርሃን ነው።
የኢትዮጵያ የማዕድን ምርት እመርታ
Aug 21, 2026 1341
በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአገር በቀል የኢኮኖሚና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ታግዞ፣ ባለፉት ዓመታት የታዩበትን የአሰራርና መዋቅራዊ ችግሮች በመቅረፍ ከፍተኛ የመነቃቃት ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ዘርፉ በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ ማዕድን በብዝኃ ዘርፍ የልማት ምልከታችን ውስጥ እና በሀገሪቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል። ባለፉት ሶስት አሥርት ዓመታት ውስጥ የማዕድን ዘርፉ ለአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያበረከተው አስተዋጽኦ ከ0 ነጥብ 8 በመቶ በታች የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ግን መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው የላቀ ትኩረት ከፍተኛ መዋቅራዊ ሽግግር እያመጣ ይገኛል። በ2018 በጀት ዓመት ከዘርፉ 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ተችሏል። ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ92 በመቶ የገቢ ዕድገትና የ27 በመቶ የምርት መጠን ብልጫ ያሳየ ሲሆን፣ ምርቶቹም በዋናነት ወደ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ አሜሪካ፣ ጀርመን እና ቻይና ተልከዋል። በወጪ ንግድ እድገት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው የወርቅ ምርት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ለውጭ ገበያ የቀረበ ሲሆን እስከ ዓመቱ ማብቂያ 32 ቶን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።   በባህላዊ መንገድ የሚመረተውን የወርቅ ምርት ለማዘመንም መንግሥት የማጣሪያና ማቀለጫ ፋብሪካዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል። የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ከውጭ የሚገቡ ስትራቴጂክ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህም ለድንጋይ ከሰል ግዢ ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት የተቻለ ሲሆን፣ የሲሚንቶ ምርትም ባለፉት ስምንት ዓመታት ከነበረበት 8 ሚሊየን ቶን አሁን ላይ በዓመት ወደ 14 ሚሊየን ቶን አድጓል። ሀገሪቱ በየዓመቱ ለማዳበሪያ ግዢ የምታወጣውን 2 ቢሊየን ዶላር ለማስቀረትም የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ተጀምሯል። በተጨማሪም በየዓመቱ ለብረት ምርት ግዢ የሚወጣውን 1 ቢሊየን ዶላር በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት የሚያስችል ግዙፍ ፋብሪካ የመገንባት ስምምነት ተፈጽሞ ወደ ስራ ተገብቷል። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በዘርፉ የተሰማሩ ፕሮጀክቶች ዋጋ 10 ቢሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከለውጡ በፊት ከነበረውና ከ100 ሚሊየን ዶላር የማይበልጡ አነስተኛ ኢንቨስትመንቶች በከፍተኛ ደረጃ የለወጠ ስኬት ነው። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በአፋር ክልል የሚገኘውን ግዙፍ የፖታሽ ክምችት ለማልማት ፈቃድ አግኝቶ ወደ ሥራ ገብቷል። በተጨማሪም ታንታለምን እሴት ጨምሮ ለመላክ ከአሜሪካ ኩባንያ ጋር ድርድር እየተደረገ ሲሆን፣ ለባትሪና ቴክኖሎጂ ወሳኝ የሆኑትን ሊቲየም፣ ኮባልትና ኒኬልን ለማምረት ዝግጅት ተጠናቋል። የኢንቨስትመንት ምህዳሩን ሳቢ ለማድረግ የማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ አሰራር ቅድሚያ የመጣን ቅድሚያ ማስተናገድ በሚል መርህ እንዲመራ ተደርጓል። የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና መላኪያ ፈቃዶች፣ እንዲሁም የካዳስተር ሲስተም ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ አሰራር ተሸጋግረዋል። በ2019 በጀት ዓመት ከዘርፉ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፣ የመንግሥት ስትራቴጂካዊ እቅድ እ.አ.አ. በ2030 የማዕድን ወጪ ንግድ ገቢን ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ በማድረስ ኢትዮጵያን ከአፍሪካ አምስት ቀዳሚ የማዕድን አምራች ሀገራት ተርታ ማሰለፍ ነው።   በዘርፉ እየተካሄደ ያለው መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ በውጭ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኝነት በመቀነስ ወደ ኢንዱስትሪ መሪነት የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥነዋል። የወርቅ፣ የተፈጥሮ ጋዝ፣ የፖታሽ እና የቴክኖሎጂ ማዕድናት በሀገር ውስጥ እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ላይ የሚኖራትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ያረጋግጣል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም