ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በምዕራብ ጎንደር ዞን ለበጋ መስኖ ልማት አስፈላጊ የግብርና ግብአቶች ቀርበዋል
Nov 28, 2025 12
ገንዳ ውኃ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ ለበጋ መስኖ ልማት የሚያስፈልጉ የግብርና ግብአቶችን በማቅረብ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን የሕብረት ሥራ ማህበራት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የመተማ ገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የአፈር ማዳበሪያ ለመስኖ ልማቱ እያቀረበ መሆኑም ተመሏክቷል። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ተወካይ ሲሳይ አለበል እንደገለጹት፣ ዞኑ ለመስኖ ልማት የሚውል ሰፊ መሬት፣ ለበጋ መስኖ ልማት የሚስማማ የአየር ንብረትና ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች ባለቤት ነው። በመሆኑም ይህን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ለበጋ መስኖ ልማት አስፈላጊ ግብአቶችን በማቅረብ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   በልማቱም የአርሶ አደሩን ዘላቂ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመረው የግብአት አቅርቦት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በመስኖ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች በየዓመቱ የግብዓት እጥረት ይገጥማቸው እንደነበር አስታውሰው፣ ዘንድሮ ችግሩን ለመፍታት በተደረገው ጥረት ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘር፣ ፀረ ተባይና ኬሚካል ቀድሞ መቅረቡን አቶ ሲሳይ ተናግረዋል። በመተማ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን የቀረበው ማዳበሪያም በበጋ መስኖ ልማት የሚሳተፉ አርሶ አደሮችን ምርታማነት በማሳደግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችል ነው። የመተማ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ ሥራ አስኪያጅ ሀብቴ ዘውዱ በበኩላቸው የበጋ መስኖ ልማትን በግብአት በመደገፍ ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ ነው። ለዚህም በተያዘው የበጋ ወቅት ለሚካሄደው የመስኖ ልማት ዩኒየኑ 2ሺህ 800 ኩንታል ዳፕ እና ዩሪያ ማዳበሪያ ማቅረቡን በማሳያነት ጠቅሰዋል። በገንዳውኃ ከተማ ዙሪያ በመስኖ ልማት የተሰማሩት አርሶ አደር አብዱ ሁሴን እንደገለጹት በልማቱ በየዓመቱ ይገጥማቸው የነበረው የማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት መፈታቱን ገልጸዋል።
ኮሌጁ የገጠሩን ማህበረሰብ ችግር ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ ነው 
Nov 28, 2025 15
ድሬደዋ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦የገጠሩን ማህበረሰብ ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት በተቀናጀ መንገድ እየሰራ መሆኑን በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ገለጸ። ኮሌጁ በታዳሽ ኃይል ልማት ከሚሰራ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በማህበር ለተደራጁ የገጠር ወጣቶች በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የእህል ወፍጮ አስረክቦ ወደ ስራ አስገብቷል። የኢትዮ -ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ወጣቱ የአካባቢውን ፀጋዎች አልምቶ እራሱንና አካባቢውን እንዲለውጥ በክህሎት የታገዘ የተለያዩ ስልጠናዎች ተዳራሽ እያደረገ ይገኛል።   በእስካሁኑ እንቅስቃሴ ለ120 ወጣቶች ክህሎት መር ስልጠና መስጠቱን ጠቅሰው በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የዘመናዊ ወፍጮ ባለቤት የተደረጉት የቃልቻ ገጠር ቀበሌ ወጣቶች የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከጀርመን ተራድኦ ድርጅት በተገኘ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የተገዛውንና በፀሐይ ሐይል የሚሰራ ወፍጮ በአይነትና በጥራት በኮሌጁ ሰርቶ ማሳያዎች (ወርክሾፖች) በማባዛት በገጠር ቀበሌዎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የገጠሩን ህብረተሰብ ማህበራዊ ችግሮች የሚፈቱትንና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ ወፍጮዎችን ለማባዛት በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ከሚሰሩ አጋር ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።   ከዚህ በተጨማሪ በገጠር ቀበሌዎች ለሚገኙ ወጣቶች የተለያዩ የክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት በፈጠራ እና በክህሎት ታግዘው የአካባቢያቸውን ሃብቶች ወደ ጥቅም እንዲለውጡ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በኤሌክትሪክ መሳሪያዎች መገጣጠምና መጠገን ስልጠና የተሰጣቸው በማህበር የተደራጁ ወጣቶች በበኩላቸው እንዳሉት፤ ኮሌጁ የገጠሩን ማህበረሰብ ችግሮችን ለመፍታት እያደረገ የሚገኘው ስራ የሚበረታታ ነው።   የማህበሩ አባል ወጣት ጀማል ኢብራሂም እንደተናገረው ፤ በፀሐይ ኃይል የሚሰራ ወፍጮ ከበቂ ስልጠና ጋር ማግኘታቸው ቀጣዩን የህይወቸውን ምዕራፍ ለመምራት ያስችላቸዋል። ይህን መሰል የተቀናጀ ድጋፍ ለወጣቶች ቢደረግ የወጣቱን ተስፋና ህይወት የበለጠ ለመለወጥ እንደሚያስችልም ነው የተናገረው።   የማህበሩ አባል ወይዘሮ ሩሚያ መሐመድ በበኩሏ፤ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰራው ወፍጮ 24 ሰአታት ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት የነበረውን ችግር ለመፍታት እንደሚያስችልም ገልጻለች ። እናቶች በውሃ እና በኤሌክትሪክ መቆራረጥ ምክንያት ይደርስባቸው የነበረውን ጫና ለመቀነስ ያግዛል ስትል ገልጻለች።
"ልወቅሽ ኢትዮጵያ" ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን እያጎለበተ ነው
Nov 28, 2025 28
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ "ልወቅሽ ኢትዮጵያ" የተሰኘው ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን በማነቃቃት በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የቱሪዝም ሚኒስቴር የፕሮሞሽን ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ተሾመ ተክሉ ለኢዜአ እንደገለጹት ልወቅሽ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ትውልዱ ስለ ሀገሩ ባህል፣ ታሪክ እና የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዲያውቅ ለማድረግ ያለመ ንቅናቄ ነው። ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በተለያዩ ከተሞች የ"ልወቅሽ ኢትዮጵያ" የሩጫ ውድድር ባለፉት ዓመታት እየተካሄደ እንደሚገኝ ለአብነት አንስተው ፕሮግራሙ በሀገር ውስጥ ቱሪዝም ላይ ትልቅ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። መርሃ ግብሩ ከሩጫው ባሻገር ልዩ የጉብኝት ፓኬጆችን በማዘጋጀት ዜጎች የተፈጥሮና የቅርስ ስፍራዎችን እንዲጎበኙ እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም በሩጫው ወቅት በሚያልፏባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ታሪካዊና ባህላዊ እሴቶችን እንዲገነዘቡ እያስቻለ መሆኑንም ጨምረው አስታውቀዋል። ውድድሩ በሚካሄድባቸው ከተሞች፣ የአካባቢው ማኅበረሰብ ከቱሪዝም ፍሰቱ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን ዕድል እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ከተሞቹ ልዩ ባህሪያቸውንና መስህቦቻቸውን ለብዙኀኑ በማስተዋወቅ የተሻለ ዕውቅና እያገኙ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ይህ የስፖርትና የቱሪዝም ትስስር የሀገር ውስጥ እንቅስቃሴን ከፍ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ ለሀገራዊ ብልጽግና የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ዳግም ተሾመ ፕሮግራሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ መምጣቱንና በአሁኑ ጊዜ በስድስት ከተሞች እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ ውድድሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲሁም የውጭ ዜጎች እየተሳተፉበት እንደሚገኙ አንስተው በርካታ ሰዎች በመርሃ ግብሩ ለማሳተፍ ፍላጎታቸውን እያሳዩ እንደሚገኙም አመልክተዋል፡፡ መርሀ ግብሩን በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞች ለማስፋት ዕቅድ መያዙንና ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በደንብ እንዲያውቁ የቱሪዝም ሀብቶችን እንዲጎበኙ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የዘንድሮው ልወቅሽ ኢትዮጵያ የሩጫ ውድድር ከጥር ጀምሮ በደብረብርሃን፣ ሀዋሳ፣ ጅማ፣ በቆጂ፣ አርባምንጭ፣ ሀረር ዲስከቨር ኢትዮጵያ ክላሲክ በሚል መሪ ቃል እንደሚካሄድ ተመላክቷል።
መስኖን ተጠቅመን ባለማነው አትክልትና ፍራፍሬ ተጠቃሚ ሆነናል-አርሶ አደሮች
Nov 28, 2025 45
ገንዳውኃ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ የበጋ መስኖን በመጠቀም ባለሙት አትክልትና ፍራፍሬ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን በልማቱ የተሳተፉ አርሶ አደሮች ገለጹ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ የነበራቸው አርሶ አደሮች እንደገለፁት፤ መስኖን በመጠቀም ባለሙት አትክልትና ፍራፍሬ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን አሳድገዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ ነዋሪው አርሶ አደር አደም ሁሴን ለኢዜአ እንደገለጹት መስኖን በመጠቀም ቋሚ አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ይገኛሉ።   ባለፉት ቅርብ ዓመታት ያለሙት የማንጎ፣ የፓፓያ፣ የዘይቱን፣ የሙዝ፣ የሎሚና የሌሎች የፍራፍሬ ዝርያዎች ምርት መስጠት በመጀመራቸው ባለፈው ዓመት ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮ ዓመትም ካለፈው የተሻለ ገቢ ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ጠቁመው ከሚያገኙት ገቢም በባንክ በመቆጠብ በቀጣይ ወደ ተሻለ ኢንቨስትመንት ለመግባት ፍላጎቱ እንዳላቸውም አስረድተዋል። ሌላኛው የዚሁ ከተማ ነዋሪ አርሶ አደር ሙሀመድ ገደፋው በበኩላቸው፤ የፍራፍሬ ልማት በቅርብ ጊዜ የተጀመረ ቢሆንም የሚሰጠውን ጥቅም በመረዳት በብዛት የማልማት ስራ እየሰራሁ ነው ብለዋል።   በሩብ ሄክታር ማሳቸው ላይ ባለሙት ፍራፍሬ በዓመት ከ150 ሺህ ብር በላይ ገቢ እያገኙ መሆኑን ጠቁመው የፍራፍሬ ልማቱን ወደ አንድ ሄክታር ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል። ቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት አዋጭ መሆኑን በመገንዘብ አንድ ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ በዘርፉ መሰማራቱን የገለፀው ደግሞ የመተማ ዮሃንስ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት ሰውበሰው አለነ ነው።   ከሁለት ሄክታር በላይ መሬት ላይ ያለማው የማንጎ፣ የፓፓያ፣ የሎሚ፣ የብርቱካንና የዘይቱን ተክል ምርት መስጠት በመጀመሩ እስካሁን ያወጣውን ወጪ በዘንድሮው የምርት ሽያጭ እንደሚመልስም ተስፋ አድርጓል። በምእራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ባለሙያ አቶ አስናቀው አራጋው እንዳሉት፤ በዞኑ አንድ ሺህ 200 ሄክታር መሬት በፍራፍሬና ቋሚ አትክልት ለምቷል። በዚህም 35 አርሶ አደሮችንና ባለሃብቶችን በማሳተፍ በተካሄደው የፍራፍሬ ልማት ባለፈው ዓመት ከ170 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።   በተያዘው በጀት ዓመትም ከ200 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ አስረድተዋል። እየተገኘ ያለውን ጥቅም በቀጣይ ለማስፋትም ዘንድሮ ከ250 ሺህ በላይ አዳዲስና ቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል ፍል የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በተጨማሪም በዞኑ የሚካሄደው የፍራፍሬ ልማት ለወጣቱ የስራ እድል መፍጠሪያ ዋና አማራጭ ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ አመልክተዋል። አርሶ አደሮች የሚፈልጉትን የፍራፍሬ ችግኝ በቀበሌና በወረዳ ማዕከላት ለማሰራጨት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተደረገልን ድጋፍ ከተረጅነት ወደ አምራችነት ተሸጋግረናል
Nov 28, 2025 35
ሰቆጣ፤ ሕዳር 19/2018(ኢዜአ)፡ - በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው የተደረገላቸው ድጋፍ በመጠቀም ከተረጅነት ወደ አምራችነት መሸጋገራቸውን በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ገለጹ። በብሔረሰብ አስተዳደሩ በተደረገላቸው ድጋፍ ውጤታማ የሆኑ ከ52 ሺህ በላይ ሰዎች ከተረጅነት መላቀቃቸውን የአስተዳደሩ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። አርሶ አደር ሞገስ ቸኮለ በብሔረሰብ አስተዳደሩ አበርገሌ ወረዳ የ01 ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፤ ላለፉት 15 ዓመታት በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው የምግብ እህል ድጋፍ ሲደረግላቸው መቆየቱን ለኢዜአ ተናግረዋል።   ይህም የዕለት ምግብ ከመሸፈን ባሻገር ጥሪት ማፍራት እንዳላስቻላቸው አውስተው፤ በቅርቡ የውሃ መሳቢያ ሞተር ድጋፍ ተደርጎላቸው አንድ ሄክታር መሬታቸው ላይ የበጋ መስኖን በመጠቀም ሽንኩርት በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው ላለፉት 10 ዓመታት ድጋፍ ሲደርግላቸው እንደቆየ በማስታወስ አስተያየታቸውን የሰጡት ደግሞ ሌላው የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ሃይሌ ጎንጠ ናቸው።   መንግስት በገነባላቸው አነስተኛ ግድብና የተደረገላቸውን የውሃ መሳቢያ ሞተር ድጋፍ በመጠቀም በግማሽ ሄክታር መሬታቸው ላይ ቲማቲምና ሽንኩርት በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። መንግስት አርሶ አደሩ በምግብ ራሱን እንዲችል እያደረገ ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመልክተዋል።   በዘላቂነት እራሳቸውን ለመቻልም በየተሰማሩበት የልማት ዘርፍ ተግተው እየሰሩ መሆኑን የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ገልጸዋል። የአበርገሌ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መሰረት ወልደየስ ፤ ከሁለት ሺህ በላይ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎችን ከተረጅነት ለማላቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከተረጅነት ለማላቀቅ የተያዘውን ግብ ለማሳካትም 78 ሚሊየን ብር የቀጥታ ድጋፍ ተደርጓል ያሉት ወይዘሮ መሰረት፤ ለ200 ተጠቃሚዎችም የውሃ መሳቢያ ሞተር ድጋፍ መደረጉንም አንስተዋል።   በብሔረሰብ አስተዳደሩ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት የምግብ ዋስትና ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ ገብረኪዳን እንደገለጹት ፤ በአስተዳደሩ በፕሮግራሙ የታቀፉ ተጠቃሚዎችን ከተረጅነት ወደ አምራችነት ለማሸጋገር የገንዘብ ድጋፍ ሲደረግላቸው ቆይቷል።   በተደረገላቸው ድጋፍ በእንስሳት እርባታ፣ በንግድና በመስኖ ልማት ተሰማርተው ውጤታማ የሆኑ ከ52 ሺህ በላይ ሰዎችን ከተረጅነት ማላቀቅ ተችሏል ብለዋል። ቀሪዎቹን በዘላቂነት ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገርም በ20 ሚሊየን ብር አምስት የመስኖ መሰረተ ልማቶች በብሔረሰብ አስተዳደሩ በመገንባት ላይ እንደሚገኙም ገልጸዋል።
የሚታይ
በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ምሕዳሩን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 
Nov 27, 2025 151
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ምሕዳሩን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አስታወቁ። "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ሲካሄድ የቆየው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል። ተቀማጭነቱን አሜሪካን ሀገር ያደረገው ግሎባል ኢንተርፕርነርሺፕ ኔትወርክ፤ ኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ ባዘጋጀቻቸው ኹነቶች ከ200 ሀገራት ጋር ተወዳድራ አንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጿል።   የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢንተርፕርነር ምህዳር ግንባታ ላይ የተከናወኑ ስራዎች በዘርፉ ውጤት እንዲመዘገብ አድርጓል። በአሁኑ ወቅት በኢንተርፕርነር ዘርፉ ላይ የተገኘው ስኬት የኢትዮጵያን አዲስ መልክና እድገት ለማስተዋወቅ የሚረዱ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ውድድር በማድረግ ከዓለም ስምንተኛ ከአፍሪካ ደግሞ ሁለተኛ በመሆን አጠናቅቃ እንደነበርም አስታውሰዋል። በዘንድሮው ዓመትም በርካታ ተቋማት በመደመር እሳቤ በዘርፉ በትብብር መስራታቸው ኢትዮጵያ ቀዳሚውን ስፍራ በመያዝ ውድድሩን እንድታጠናቅቅ አድርጓል ነው ያሉት።   በአጭር ጊዜ ውስጥ የኢንተርፕርነር ዘርፍ ምህዳርን በማስፋት ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ ተችሏል ያሉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ፤ በቅንጅት ከተሰራ የኢትዮጵያን እድገት ለማሳካት እንደማያዳግትም አመላካች መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በውድድሩ ያስመዘገበችው ውጤት ኢንቨስትመንትን ከመሳብ ባሻገር ችግር ፈቺ ኢንተርፕርነሮችን እና በዘርፉ ምርምር የሚያደርጉ አካላትን ለማፍራት እንደሚረዳ አብራርተዋል፤ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሀሰን ሁሴን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በዘንድሮው ዓመት ኢንተርፕነር ዘርፉን ለመለወጥ በጋራ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል። ይህንን ጥረት በማጠናከርም በቀጣይ በተለይ የዘርፉን ምህዳር የማስፋት ስራን ስኬታማ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውም ነው ጥሪያቸውን ያስተላለፉት ።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 27, 2025 125
አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 18/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያን ቁልፍ የትኩረት መስኮች ባማከለ መልኩ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የአፍሪካ የፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሞሮኮ ራባት ተካሄዷል። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከፎረሙ ጎን ለጎን ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ የበጀት ድጋፍን ማጠናከር፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ጨምሮ በሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የተቀናጀ የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲኖር ማድረግ እና ኢትዮጵያ የምታዘጋጀውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ በፋይናንስ መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ያላቸው የቆየ አጋርነትም በውይይቱ ላይ ተነስቷል። የገንዘብ ሚኒስትሩ ባንኩ ለኢትዮጵያ የልማት ስራዎች እየተወጣ ያለውን ወሳኝ ሚናም አንስተዋል። ባንኩ የኢትዮጵያን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በፋይናንስ ለመደገፍ ያለውን ዝግጁነት አድንቀዋል። የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የሪፎርም ሂደት ያደነቁ ሲሆን ባንኩ በኢትዮጵያ የግል ኢንቨስትመንትን በሚያሳድጉ እና የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት በሚፈጥሩ መስኮች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍ ለማጠናከር ፍላጎት እንዳለው አመልክተዋል። የገንዘብ ሚኒስትሩ እና የባንኩ ፕሬዝዳንት በውይይቱ ላይ ተከታታይና የቴክኒክ ምክክሮችን ለማጠናከር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን በዘላቂ ልማት፣ ቀጣናዊ ትስስር እና የግሉ ዘርፍ እድገት በሚያጠናክር መልኩ ለማጎልበት እንደሚሰሩ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
ኢትዮ ቴሌኮም ሶስተኛውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት አስጀመረ
Nov 27, 2025 139
አዲስ አበባ፤ ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም ሶስተኛውንና እጅግ ፈጣን የሆነውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት በአዲስ አበባ አስጀምሯል። ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ሰሚት በተለምዶ ፍየል ቤት አካባቢ ያስገነባውን ሶሰተኛውን ዘመናዊና ፈጣን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት የኢት ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ እንዳሉት ጣቢያው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መጠቀምን የሚያበረታታና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የተጀመረው ጥረት አንዱ አካል ነው።   ኢትዮ ቴሌኮም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ከማድረግ በተጨማሪ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን ገልፀው፤ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ መሙያ ጣቢያ ግንባታ የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የባትሪ መሙያ ጣቢያው የተገጠመለት ቴክኖሎጂ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና አስተማማኝ መሆኑን ጠቁመዋል። እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) ቴክኖሎጂ የባትሪ መስፈርቶችን በመተንተን እንዲሁም የባትሪውን ደህንነት በመፈተሽ የተሽከርካሪውን ባትሪ በፍጥነት ቻርጅ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል። ከዚህ በፊት ተቋሙ በተከላቸው ሁለት የባትሪ መሙያ ማዕከላት ከ165 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች የኤሌክትሪክ ቻርጅ መጠቀማቸውን ጠቁመዋል። ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያው በአንድ ጊዜ 16 ተሽከርካሪዎች ባትሪ እንዲሞሉ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው፤ አንድ መኪና በ15 ደቂቃ ባትሪውን መሙላት እንደሚችል ተናግረዋል።
3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ መካሄዱ የኢትዮጵያን የልማት ስኬቶችና ቀጣናዊ ሚናዋን አጉልቶ ለማሳየት መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል
Nov 27, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ 3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ መካሄዱ የኢትዮጵያን የልማት ስኬቶችና ቀጣናውን ለማስተሳሰር እያከናወነቻቸው ያሉ ውጤታማ ተግባራትን አጉልቶ ለማሳየት መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ኢጋድ ኢትዮጵያ የዘንድሮውን የሚዲያ አዋርድ እንድታስተናግድ መምረጡ በአረንጓዴ ዐሻራ እና ሌሎች የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራዎች ላከናወነቻቸው ስኬታማ ተግባራት እውቅና የሰጠ መሆኑንም ገልጿል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በሰጡት መግለጫ የሚዲያ ሽልማቱ ከአረንጓዴ ልማትና ከአየር ንብረት ጥበቃ ጋር በተያየዙ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሽልማት መርኃ ግበሩን ለማዘጋጀት መመረጧ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ አመራር ውስጥ እያበረከተች ላለው ቁልፍ ሚና እውቅና የሰጠ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ሁለተኛውን የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ስኬታማ በሆነ መንገድ ማስተናገዷእንዲሁም የኮፕ-32 ጉባኤን እንድታዘጋጅ ለመመረጧ እውቅና የሰጠ ምርጫ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ሽልማቱ የቀጣናውን የሚዲያ ባለሙያዎች ለማቀራረብና ቀጣናዊ ትስስሮችን ለማጠናከር የሚካሄድ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡበት ጊዜም የልማት ስኬቶችን የማስተዋወቅ፣ ኢትዮጵያ ለቀጣናው ትስስር እያከናወነቻቸው ያሉ ስራዎችን አጉልቶ ለማሳየት መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ በዘንድሮው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት የትኩረት መስከ በሆነው የአረንጓዴ ልማት ሥራ በአርዓያነት የሚወሰዱ ሥራዎችን አከናውናለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ቀጣናዊና አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ሆኗል፡፡ የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ውድድሩ በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ፣ በህትመት፣ በዲጂታል ሚዲያ እና የሴቶች ዘርፍን ጨምሮ በስምንት መስኮች እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡ 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ለውድድር ያስገቡ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡ የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱ በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና የሚጫወት ነው፡፡

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
አመራሩ ትብብርና አብሮነቱን በማጠናከር ለልማት መትጋት አለበት
Nov 27, 2025 124
ሀዋሳ፤ ሕዳር 18/2018 (ኢዜአ) ፡- በየደረጃው ያለው አመራር በተግባርና አስተሳሰብ ትብብርና አብሮነቱን በማጠናከር ለልማትና ለሕዝብ አገልግሎት መትጋት አለበት ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ አስገነዘቡ። "በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ላለፉት ዘጠኝ ቀናት በሀዋሳ ከተማ ለክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል። ስልጠናው መጠናቀቁን ተከትሎ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እንደገለጹት፤ አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን ዕውቀት በአግባቡ ወደ ተግባር በመለወጥ በክልሉ የተጀመረውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ ዕውን ለማድረግ ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል።   በየደረጃው ያለው አመራር በተግባርና አስተሳሰብ ትብብርና አብሮነቱን በማጠናከር ለልማትና ለሕዝብ አገልግሎት መትጋት አለበት ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማት ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት መውጣት የጋራ ግብ አድርገን በትብብር መስራት አለብን ብለዋል። በክልሉ በሁሉም መስኮች ተስፋ የተሰነቀባቸው የልማት እንቅስቃሴዎች እንዳሉ አንስተው፤ እነዚህን ከዳር ማድረስና ለስኬት ማብቃት ይገባል ሲሉም አክለዋል። በከተሞች የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ስራና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በአግባቡ በማስፋፋት ከተሞችን የብልጽግና ማዕከል የማድረግ ስራ አፅንኦት የተሰጠው ተግባር መሆኑንም አንስተዋል። የሴቶችንና የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጥና አሳታፊ የግብርናና ገጠር ልማት ስራዎችን በማጠናከር ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ርብርብ ማድረግም እንዲሁ።   በክልሉ በተለይም የአገልግሎት፣ የኢንዱስትሪ፣ የቱሪዝም፣ የዲጅታላይዜሽንና ሌሎችም የልማት ተግባራት ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል። በንግዱ ዘርፍ የሚስተዋለውን ሕገወጥነት በመከላከል የዋጋ ንረትን የማርገብና ገበያን የማረጋጋት ተግባርም ልዩ ትኩረት ይደረግበታል ብለዋል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን መፍታት የሚያስችለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል። በዚህ ሁሉ ሂደትም አመራሩ በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መስራትና እቅዶቹን ለውጤት ማብቃት ይጠበቅበታል በማለት አስገንዝበዋል።
ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Nov 27, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክትን በመገንባት ሕብረ ብሔራዊ አንድነት እና የፌዴራሊዝም ሥርዓትን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ተገለጸ። "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ 47ኛው የጉሚ በለል መድረክ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰአዳ አብዱራህማን ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ለብዙ ዓመታት ያደረጉት ትግል ለሁሉም የምትሆን፣ ሁሉንም የምትመስል እና ሁሉንም በእኩልነት የምታስተናግድ ሀገር ለመገንባት ነው ብለዋል።   ይህንን በተግባር ለማረጋገጥ በተለይ የለውጡ መንግስት የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ባሕል፣ ወግ እና ታሪክ እንዲከበር በማድረግ የጋራ ትርክትን እያጠናከረ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም አቅጣጫ የገዘፈ ታሪክ፣ ውብ ማንነት፣ ብዝኃ መልክ፣ ባሕል፣ ቋንቋና እሴት ያላት፤ በልዩነት ውስጥ ባለው ውበትና አንድነት የምትደምቅ ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። በልዩነት ውስጥ ያለውን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት በጋራ ትርክት በማጠናከር ሀገርና ሀገራዊ እሴትን ለመገንባት መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ አሰባሳቢ የሆኑ የጋራ ትርክትን በመገንባት ሕብረብሔራዊ አንድነትና የፌዴራሊዝም ሥርዓትን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙም ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ በባኩላቸው እንደተናገሩት፤ በነጠላ ትርክት የተፈጠሩ ችግሮችን በመፍታት ወደ ዴሞክራሲ የሚደረገው ሽግግር ተስፋ ሰጪ ነው።   ተግዳሮቶችን በሀገራዊ ምክክር ለመፍታት እየተሰራ ያለው ተግባር የጋራ ትርክትን ይበልጥ ለማጠናከር የላቀ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል መከበር እህትማማችነትና ወንድማማችነትን ከማጠናከር ጎን ለጎን ነጠላ ትርክት በማሸነፍ እንደ ክልልም ሆነ እንደ ሀገር የጋራ ትርክት ለመገንባት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ጠንካራ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና ፌዴራሊዝምን በአስተማማኝ መሰረት ላይ የመገንባት ታላቅ ግብን ለማሳካት እየተደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ ሁሉም የበኩሉን መወጣት እንደሚጠበቅበትም አንስተዋል። በመድረኩ ላይ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎችን አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አመራሩ  ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል 
Nov 27, 2025 98
ሰመራ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አመራሩ በግንባር ቀደምትነት ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ተናገሩ። በሠመራ ከተማ "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ለአፋር ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በሁለተኛ ዙር ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል። በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ፤በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አመራሩ በግንባር ቀደምትነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል።   በክልሉ የልማት ተግባራት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና የህብረተሰብን ፍላጎት ባገናዘበ መልኩ መሰራታቸውን ተናግረዋል። በክልሉ እየተከናወነ ያለው ልማት ተስፋ ሰጪና የክልሉን የመበልጸግ አቅም ያሳየ መሆኑንም ጠቁመዋል። ለውጡን ተከትሎ በክልሉ የተሰሩት የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አመራሩ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም በስልጠናው የተገኘውን ተሞክሮ በማስፋት ለበለጠ ስራ መትጋት እንደሚገባ ተናግረዋል። በስልጠናው ከክልል፣ ከዞኖችና ወረዳዎች የተውጣጡ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን ከስልጠናው ጎን ለጎን የተሰሩ የልማት ስራዎችንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ዘርፈ ብዙ ውጤቶች የተገኙባቸው ልማቶች ተከናውነዋል- ከንቲባ ከድር ጁሃር
Nov 27, 2025 98
ድሬዳዋ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦በድሬዳዋ የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ እና ዘርፈ ብዙ ውጤቶች የተገኘባቸው ልማቶች ተከናውነዋል ሲሉ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። "በመደመር መንግስት እይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የአስተዳደሩ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ያካሄዱትን ስልጠና ዛሬ ያጠናቀቁ ሲሆን አመራሮቹ በአስተዳደሩ የተከናወኑ ልማቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በተጨማሪም በደም ዕጦት አንድም ሰው መሞት እንደሌለበት መልዕክት በማስተላለፍ በአርአያነት ደም ለግሰዋል። በስልጠናው ማጠቃላይ ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ እና ዘርፈ ብዙ ውጤቶች የተገኘባቸው ልማቶች ተከናውነዋል ብለዋል።   በግብርና ፣ በኢንዱስትሪ፣ በኮሪደር ልማት፣ በቴክኖሎጂ እና በቱሪዝም ዘርፎች እየተመዘገቡ የሚገኙ ሁለንተናዊ ውጤቶችን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል ርብርቡ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል። በተለይም ከተማዋን ለስራና ለኑሮ ምቹ እያደረገ የሚገኘው የኮሪደር ልማት በስፋት እንደሚቀጥል ጠቅሰው በአራቱ የገጠር ክላስተሮች እና በደቻቱ ወንዝ ዳርቻዎችም የኮሪደር ልማቱ በቅርቡ እንደሚጀመር ተናግረዋል። በመሆኑም አመራሩ የተገኙ ውጤቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና የሚጀመሩ አዳዲስ ዘርፎችን በቁርጠኝነት ዳር ለማድረስ የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል። ለአመራሩ የተሰጠው ስልጠና ተልዕኮን በታላቅ ብቃትና ቁርጠኝነት ለመፈፀም ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው የገለፁት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ናቸው።   በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በፈጠራና በፍጥነት መርህ የብልጽግና ትልሞችን ሙሉ በሙሉ በማሳካት ድሬዳዋ የንግድ፣ የኢንዱስትሪ እና የኢንቨስትመንት መዳረሻ እና የዜጎች ብልፅግና የተረጋገጠባት ለማድረግ የጀመሩትን ስራ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በስልጠናው እና በጉብኝቱ የተካፈሉ አመራሮች በበኩላቸው፤ የሃሳብና የተግባር አንድነትን በማፅናት እየተመዘገቡ የሚገኙ ሁለንተናዊ የልማት ውጤቶችን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ ስልጠናው ቁጭትና መነሳሳት እንደፈጠረባቸው ለኢዜአ ገልጸዋል። በአርአያነት ደም የለገሱት የስልጠናው ተሳታፊ አቶ አብዶ ሙሜ እና ወይዘሮ ስሜነሽ አለማየሁ እንዳሉት፤ ያላቸውን አቅም አሟጠው በመጠቀም እየተመዘጉ የሚገኙትን ውጤቶች ለማሳደግ ተዘጋጅተዋል። በተለይም በጉብኝቱ ወቅት በአስተዳደሩ ገጠርና ከተማ ክላስተሮች የተሰሩት የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት በትክክል እያረጋገጡ እንደሆኑ መመልከታቸው የበለጠ እንዲተጉ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።
የአመራሩን አቅም በማጎልበት የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ
Nov 27, 2025 98
ወላይታ ሶዶ፤ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአመራሩን አቅም በማጎልበት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች እንደሚጠናከሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። "በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ መካከለኛና ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል። በስልጠናው ማጠቃለያ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት፤ በክልሉ የአመራሩን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በማቀናጀት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው።   ባለፉት ጊዜያት ለአመራሩ የተሰጡ ስልጠናዎች በክልሉ ዘለቂ እድገት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ጠቅሰው በሁሉም መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው አመራሩን የማብቃት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ሁሉን አቀፍ ዕውቀት ያለው አመራር ከመፍጠር ባለፈ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በማምጣት የህዝብ ጥያቄን የመመለስ አቅም ማሳደግ እንደሚገባም አመልክተዋል። በክልሉ ህብረብሔራዊነትን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ በቅንጅት የሚሰራው ሥራ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ከስልጠናው ተሳታፊ አመራሮች መካከል አቶ ዳኘ ሂዶ፤ ስልጠናው አመራሩ ራሱን እንዲመለከትና የአካባቢውን ዕምቅ አቅም አሟጦ በመጠቀም ለህዝብ ተጠቃሚነት በትጋት እንዲሰራ ያስገነዘበና አቅም የፈጠረ ነው ብለዋል።   በቀጣይም በተቋማቸው የሀሳብና የተግባር አንድነትን በማቀናጀት ለስኬታማነት ተግተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ሌላኛው ሰልጣኝ ወይዘሮ መስከረም ወልደማርያም በበኩላቸው፤ ስልጠናው በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች እንደሀገርና እንደ ክልል ያለውን አቅም ተረድተን ውጤታማ ሥራ ለመስራት እውቀት ያስጨበጠን ነው ብለዋል፡፡ በስልጠና ያገኙትን አቅም ተጠቅመው የክልሉን ጸጋ ለይቶ በማልማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተግተው እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።
በክልሉ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 27, 2025 93
ጋምቤላ፤ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የልማት እቅዶችን በቅንጅት በመተግበር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ አስታወቁ። ‎"በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በጋምቤላ ከተማ ሲሰጥ የቆየው የ2ኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል።   ‎ርዕሰ መስተደድሯ አለሚቱ ኡሞድ በአቅም ግንባታ ስልጠናው ማጠቃለያ ላይ እንዳሉት፡ የክልሉን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት በማልማት የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ‎የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያዌዎች ምላሽ ለመስጠትም በግብርና፣ በቱሪዝም፣በኢንዱስትሪና በሌሎችም ዘርፎች ያሉትን ሰፊ የመልማት አቅሞች መጠቀም ይገባል ብለዋል። ‎ለዚህም አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን አቅምና ልምዱን ወደ ተግባር በመለወጥ የክልሉን ሁለንተናዊ እድገት ማሳካት እንደሚገባም አክለዋል።   አመራሩ ህዝቡን በማስተባበር በተለይም የግብርናውን ልማት በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ላይ እየተከናወኑ ያሉትን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። አመራሩ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በመፀየፍ ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት አርአያ መሆን እንደሚገባውም አሳስበዋል። ‎አመራሮቹ በዘጠኝ ቀናት ቆይታቸው በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተሞች ልማትና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና መከታተላቸው ተገልጿል።
በሥልጠና ያገኛችሁትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለውጥ የሚያመጣ፣ እሴት የሚጨምር ሥራ መሥራት ይጠበቅባችኋል - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Nov 27, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ መሪዎች በሥልጠና ያገኛችሁትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለውጥ የሚያመጣ፣ እሴት የሚጨምር ሥራ መሥራት ይጠበቅባችኋል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ አስገነዘቡ። "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ መልዕክት ለአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ሥልጠና እየተሰጠ ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ እስካሁን በተሰጡ የሥልጠና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡ ሲሆን በሥልጠና ያገኛችሁትን ዕውቀት ወደ ተግባር መቀየር ከቻላችሁ ለውጥ ማምጣት ይቻላል ብለዋል።   የግብርናውን ዘርፍ መለወጥ ግድ እንደሚል ጠቁመው ኋላ ቀር የማረሻ ዘዴንና የአስተራረስ መንገድን በቴክኖሎጂ መቀየር እንደሚገባም ተናግረዋል። መሪዎች ለውጥ የሚያመጣ፣ እሴት የሚጨምር ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመው በግብርናው ዘርፍ ለውጥ ሲመጣ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማምጣት ቀዳሚው ጉዳይ ዘመናዊ ግብርናን መፍጠር አስፈላጊ ነው ብለዋል። ከፍጆታ አልፎ ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚኾንና ለውጭ ገበያ የሚያቀርቡ አርሶ አደሮችን መፍጠር እንደሚገባም አመላክተዋል። ሕልማችንን ማሳካት የሚያስችል ጸጋ አለን፣ መሬት፣ አየር፣ የማዕድን ሃብት፣ ትኩስ ጉልበት ያለው ወጣትና ሌሎች ሃብቶች አሉንም ብለዋል። ኢንዱስትሪን መለማመድ፣ የሚጠይቀውን አቅም በመጠቀም ውጤታማ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ከተሜነትንና የከተማ ዕድገትን በአግባቡ መምራት እንደሚያስፈልግም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።   ለቱሪዝም ዘርፉ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግ ጠቁመው አንዱ የምጣኔ ሃብት ማሳለጫ አድርጎ መሥራት እንደሚገባም አመላክተዋል። የቱሪዝም ሃብቶችን መለየት፣ መጠበቅ፣ ማልማትና ለጥቅም ማዋል እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎችን በውጤታማነት እንዲመሩና ለመስኖ ልማት፣ ለእንስሳት መኖ ዝግጅት ትኩረት እንዲሰጥም አሳስበዋል። የተፈጥሮ ሃብት ልማትን በተመለከተም ለማዕድን ሃብት ልማት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል። የንግድ ሥርዓቱን በተመለከተም ሕገ ወጥነትን፣ ኮንትሮባንድን መቆጣጠርና የገበያ ማዕከላትን መገንባት እንደሚገባ መግለጻቸውን አሚኮ ዘግቧል። የሰው ሃብት ልማታችን ላይ እንሥራ ያሉት አቶ አረጋ ከበደ የትምህርት ተቋማት መገንባት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። ማህበረሰቡ የጤና መድኅን ተጠቃሚ እንዲሆን በትኩረት እንዲሠሩና የሴቶችን፣ የወጣቶችን፣ የሕጻናትንና የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መሥራት እንደሚጠበቅም አመላክተዋል። አገልግሎት አሰጣጥ ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበው አገልጋዮች በጊዜ እና በቦታቸው ተገኝተው ለሕዝብ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡም አስገንዝበዋል። የሪፎርም ሥራን በውጤታማነት እንዲተገብሩና ስምንቱ ሪጂዮፖሊታን ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማስጀመርና ሌሎች ከተሞችም አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በቡድን-20 አባል አገሮች ጉባኤ ላይ ያደረገችው ተሳትፎ የላቀ ዲፕሎማሲ ስኬት የተመዘገበበት ነው
Nov 27, 2025 142
አዲስ አበባ፤ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በቡድን-20 አባል አገሮች ጉባኤ ላይ ያደረገችው ተሳትፎ የላቀ ዲፕሎማሲ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለጹ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ዋና ዋና የዲፕሎማሲ ስራዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው፥ ኢትዮጵያ የ2027 የኮፕ-32 (COP-32) ጉባዔን እንድታዘጋጅ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥን ለመግታት ለወሰደቻቸው እርምጃዎች እውቅና የሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ዓለም አቀፍ እውቅና እያገኘ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በኮሪደር ልማት፣ ንጹህ እና አረንጓዴ ከተሞችን ለማስፋፋት ለወሰደቻቸው ትላልቅ እርምጃዎች እውቅና የሰጠ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በስኬት ማስተናገዷ ለመመረጧ ሌላኛው ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የኮፕ-32 አስተናጋጅ ሆና መመረጧ በዲፕሎማሲው መድረክ ያላት ተሰሚነት ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል። ይህም የኢትዮጵያን በጎ ገጽታዎች ለማስተዋወቅና ለቱሪዝም ዕድገት ከፍተኛ ትርጉም ያለው መሆኑንም አስታውቀዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ-32) ተወካይ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የቡድን-20 ጉባኤ ላይ በመሳተፍ የዲፕሎማሲ ስኬት ማስመዝገቧን ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ባደረጉት ንግግር የአፍሪካን ሁነኛ አጀንዳዎችን ማንጸባረቃቸውንም አስታውሰዋል። ከበርካታ ሀገራትና የተለያዩ ተቋማት መሪዎች ጋር ስኬታማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቁመው፤ በዚህም የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል። በዚህም የልማት አጋርነት፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ጉዳዮችን ጨምሮ በበርካታ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን አንስተዋል። ይህም የኢትዮጵያ የላቀ የዲፕሎማሲ ከፍታ የተገለጸበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
ፖለቲካ
አመራሩ ትብብርና አብሮነቱን በማጠናከር ለልማት መትጋት አለበት
Nov 27, 2025 124
ሀዋሳ፤ ሕዳር 18/2018 (ኢዜአ) ፡- በየደረጃው ያለው አመራር በተግባርና አስተሳሰብ ትብብርና አብሮነቱን በማጠናከር ለልማትና ለሕዝብ አገልግሎት መትጋት አለበት ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ አስገነዘቡ። "በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ላለፉት ዘጠኝ ቀናት በሀዋሳ ከተማ ለክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል። ስልጠናው መጠናቀቁን ተከትሎ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እንደገለጹት፤ አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን ዕውቀት በአግባቡ ወደ ተግባር በመለወጥ በክልሉ የተጀመረውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ ዕውን ለማድረግ ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል።   በየደረጃው ያለው አመራር በተግባርና አስተሳሰብ ትብብርና አብሮነቱን በማጠናከር ለልማትና ለሕዝብ አገልግሎት መትጋት አለበት ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማት ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት መውጣት የጋራ ግብ አድርገን በትብብር መስራት አለብን ብለዋል። በክልሉ በሁሉም መስኮች ተስፋ የተሰነቀባቸው የልማት እንቅስቃሴዎች እንዳሉ አንስተው፤ እነዚህን ከዳር ማድረስና ለስኬት ማብቃት ይገባል ሲሉም አክለዋል። በከተሞች የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ስራና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በአግባቡ በማስፋፋት ከተሞችን የብልጽግና ማዕከል የማድረግ ስራ አፅንኦት የተሰጠው ተግባር መሆኑንም አንስተዋል። የሴቶችንና የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጥና አሳታፊ የግብርናና ገጠር ልማት ስራዎችን በማጠናከር ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ርብርብ ማድረግም እንዲሁ።   በክልሉ በተለይም የአገልግሎት፣ የኢንዱስትሪ፣ የቱሪዝም፣ የዲጅታላይዜሽንና ሌሎችም የልማት ተግባራት ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል። በንግዱ ዘርፍ የሚስተዋለውን ሕገወጥነት በመከላከል የዋጋ ንረትን የማርገብና ገበያን የማረጋጋት ተግባርም ልዩ ትኩረት ይደረግበታል ብለዋል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን መፍታት የሚያስችለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል። በዚህ ሁሉ ሂደትም አመራሩ በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መስራትና እቅዶቹን ለውጤት ማብቃት ይጠበቅበታል በማለት አስገንዝበዋል።
ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Nov 27, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክትን በመገንባት ሕብረ ብሔራዊ አንድነት እና የፌዴራሊዝም ሥርዓትን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ተገለጸ። "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ 47ኛው የጉሚ በለል መድረክ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰአዳ አብዱራህማን ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ለብዙ ዓመታት ያደረጉት ትግል ለሁሉም የምትሆን፣ ሁሉንም የምትመስል እና ሁሉንም በእኩልነት የምታስተናግድ ሀገር ለመገንባት ነው ብለዋል።   ይህንን በተግባር ለማረጋገጥ በተለይ የለውጡ መንግስት የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ባሕል፣ ወግ እና ታሪክ እንዲከበር በማድረግ የጋራ ትርክትን እያጠናከረ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም አቅጣጫ የገዘፈ ታሪክ፣ ውብ ማንነት፣ ብዝኃ መልክ፣ ባሕል፣ ቋንቋና እሴት ያላት፤ በልዩነት ውስጥ ባለው ውበትና አንድነት የምትደምቅ ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። በልዩነት ውስጥ ያለውን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት በጋራ ትርክት በማጠናከር ሀገርና ሀገራዊ እሴትን ለመገንባት መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ አሰባሳቢ የሆኑ የጋራ ትርክትን በመገንባት ሕብረብሔራዊ አንድነትና የፌዴራሊዝም ሥርዓትን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙም ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ በባኩላቸው እንደተናገሩት፤ በነጠላ ትርክት የተፈጠሩ ችግሮችን በመፍታት ወደ ዴሞክራሲ የሚደረገው ሽግግር ተስፋ ሰጪ ነው።   ተግዳሮቶችን በሀገራዊ ምክክር ለመፍታት እየተሰራ ያለው ተግባር የጋራ ትርክትን ይበልጥ ለማጠናከር የላቀ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል መከበር እህትማማችነትና ወንድማማችነትን ከማጠናከር ጎን ለጎን ነጠላ ትርክት በማሸነፍ እንደ ክልልም ሆነ እንደ ሀገር የጋራ ትርክት ለመገንባት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ጠንካራ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና ፌዴራሊዝምን በአስተማማኝ መሰረት ላይ የመገንባት ታላቅ ግብን ለማሳካት እየተደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ ሁሉም የበኩሉን መወጣት እንደሚጠበቅበትም አንስተዋል። በመድረኩ ላይ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎችን አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አመራሩ  ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል 
Nov 27, 2025 98
ሰመራ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አመራሩ በግንባር ቀደምትነት ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ተናገሩ። በሠመራ ከተማ "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ለአፋር ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በሁለተኛ ዙር ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል። በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ፤በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አመራሩ በግንባር ቀደምትነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል።   በክልሉ የልማት ተግባራት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና የህብረተሰብን ፍላጎት ባገናዘበ መልኩ መሰራታቸውን ተናግረዋል። በክልሉ እየተከናወነ ያለው ልማት ተስፋ ሰጪና የክልሉን የመበልጸግ አቅም ያሳየ መሆኑንም ጠቁመዋል። ለውጡን ተከትሎ በክልሉ የተሰሩት የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አመራሩ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም በስልጠናው የተገኘውን ተሞክሮ በማስፋት ለበለጠ ስራ መትጋት እንደሚገባ ተናግረዋል። በስልጠናው ከክልል፣ ከዞኖችና ወረዳዎች የተውጣጡ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን ከስልጠናው ጎን ለጎን የተሰሩ የልማት ስራዎችንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ዘርፈ ብዙ ውጤቶች የተገኙባቸው ልማቶች ተከናውነዋል- ከንቲባ ከድር ጁሃር
Nov 27, 2025 98
ድሬዳዋ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦በድሬዳዋ የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ እና ዘርፈ ብዙ ውጤቶች የተገኘባቸው ልማቶች ተከናውነዋል ሲሉ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። "በመደመር መንግስት እይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የአስተዳደሩ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ያካሄዱትን ስልጠና ዛሬ ያጠናቀቁ ሲሆን አመራሮቹ በአስተዳደሩ የተከናወኑ ልማቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በተጨማሪም በደም ዕጦት አንድም ሰው መሞት እንደሌለበት መልዕክት በማስተላለፍ በአርአያነት ደም ለግሰዋል። በስልጠናው ማጠቃላይ ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ እና ዘርፈ ብዙ ውጤቶች የተገኘባቸው ልማቶች ተከናውነዋል ብለዋል።   በግብርና ፣ በኢንዱስትሪ፣ በኮሪደር ልማት፣ በቴክኖሎጂ እና በቱሪዝም ዘርፎች እየተመዘገቡ የሚገኙ ሁለንተናዊ ውጤቶችን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል ርብርቡ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል። በተለይም ከተማዋን ለስራና ለኑሮ ምቹ እያደረገ የሚገኘው የኮሪደር ልማት በስፋት እንደሚቀጥል ጠቅሰው በአራቱ የገጠር ክላስተሮች እና በደቻቱ ወንዝ ዳርቻዎችም የኮሪደር ልማቱ በቅርቡ እንደሚጀመር ተናግረዋል። በመሆኑም አመራሩ የተገኙ ውጤቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና የሚጀመሩ አዳዲስ ዘርፎችን በቁርጠኝነት ዳር ለማድረስ የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል። ለአመራሩ የተሰጠው ስልጠና ተልዕኮን በታላቅ ብቃትና ቁርጠኝነት ለመፈፀም ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው የገለፁት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ናቸው።   በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በፈጠራና በፍጥነት መርህ የብልጽግና ትልሞችን ሙሉ በሙሉ በማሳካት ድሬዳዋ የንግድ፣ የኢንዱስትሪ እና የኢንቨስትመንት መዳረሻ እና የዜጎች ብልፅግና የተረጋገጠባት ለማድረግ የጀመሩትን ስራ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በስልጠናው እና በጉብኝቱ የተካፈሉ አመራሮች በበኩላቸው፤ የሃሳብና የተግባር አንድነትን በማፅናት እየተመዘገቡ የሚገኙ ሁለንተናዊ የልማት ውጤቶችን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ ስልጠናው ቁጭትና መነሳሳት እንደፈጠረባቸው ለኢዜአ ገልጸዋል። በአርአያነት ደም የለገሱት የስልጠናው ተሳታፊ አቶ አብዶ ሙሜ እና ወይዘሮ ስሜነሽ አለማየሁ እንዳሉት፤ ያላቸውን አቅም አሟጠው በመጠቀም እየተመዘጉ የሚገኙትን ውጤቶች ለማሳደግ ተዘጋጅተዋል። በተለይም በጉብኝቱ ወቅት በአስተዳደሩ ገጠርና ከተማ ክላስተሮች የተሰሩት የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት በትክክል እያረጋገጡ እንደሆኑ መመልከታቸው የበለጠ እንዲተጉ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።
የአመራሩን አቅም በማጎልበት የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ
Nov 27, 2025 98
ወላይታ ሶዶ፤ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአመራሩን አቅም በማጎልበት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች እንደሚጠናከሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። "በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ መካከለኛና ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል። በስልጠናው ማጠቃለያ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት፤ በክልሉ የአመራሩን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በማቀናጀት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው።   ባለፉት ጊዜያት ለአመራሩ የተሰጡ ስልጠናዎች በክልሉ ዘለቂ እድገት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ጠቅሰው በሁሉም መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው አመራሩን የማብቃት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ሁሉን አቀፍ ዕውቀት ያለው አመራር ከመፍጠር ባለፈ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በማምጣት የህዝብ ጥያቄን የመመለስ አቅም ማሳደግ እንደሚገባም አመልክተዋል። በክልሉ ህብረብሔራዊነትን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ በቅንጅት የሚሰራው ሥራ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ከስልጠናው ተሳታፊ አመራሮች መካከል አቶ ዳኘ ሂዶ፤ ስልጠናው አመራሩ ራሱን እንዲመለከትና የአካባቢውን ዕምቅ አቅም አሟጦ በመጠቀም ለህዝብ ተጠቃሚነት በትጋት እንዲሰራ ያስገነዘበና አቅም የፈጠረ ነው ብለዋል።   በቀጣይም በተቋማቸው የሀሳብና የተግባር አንድነትን በማቀናጀት ለስኬታማነት ተግተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ሌላኛው ሰልጣኝ ወይዘሮ መስከረም ወልደማርያም በበኩላቸው፤ ስልጠናው በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች እንደሀገርና እንደ ክልል ያለውን አቅም ተረድተን ውጤታማ ሥራ ለመስራት እውቀት ያስጨበጠን ነው ብለዋል፡፡ በስልጠና ያገኙትን አቅም ተጠቅመው የክልሉን ጸጋ ለይቶ በማልማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተግተው እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።
በክልሉ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 27, 2025 93
ጋምቤላ፤ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የልማት እቅዶችን በቅንጅት በመተግበር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ አስታወቁ። ‎"በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በጋምቤላ ከተማ ሲሰጥ የቆየው የ2ኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል።   ‎ርዕሰ መስተደድሯ አለሚቱ ኡሞድ በአቅም ግንባታ ስልጠናው ማጠቃለያ ላይ እንዳሉት፡ የክልሉን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት በማልማት የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ‎የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያዌዎች ምላሽ ለመስጠትም በግብርና፣ በቱሪዝም፣በኢንዱስትሪና በሌሎችም ዘርፎች ያሉትን ሰፊ የመልማት አቅሞች መጠቀም ይገባል ብለዋል። ‎ለዚህም አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን አቅምና ልምዱን ወደ ተግባር በመለወጥ የክልሉን ሁለንተናዊ እድገት ማሳካት እንደሚገባም አክለዋል።   አመራሩ ህዝቡን በማስተባበር በተለይም የግብርናውን ልማት በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ላይ እየተከናወኑ ያሉትን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። አመራሩ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በመፀየፍ ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት አርአያ መሆን እንደሚገባውም አሳስበዋል። ‎አመራሮቹ በዘጠኝ ቀናት ቆይታቸው በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተሞች ልማትና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና መከታተላቸው ተገልጿል።
በሥልጠና ያገኛችሁትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለውጥ የሚያመጣ፣ እሴት የሚጨምር ሥራ መሥራት ይጠበቅባችኋል - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Nov 27, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ መሪዎች በሥልጠና ያገኛችሁትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለውጥ የሚያመጣ፣ እሴት የሚጨምር ሥራ መሥራት ይጠበቅባችኋል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ አስገነዘቡ። "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ መልዕክት ለአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ሥልጠና እየተሰጠ ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ እስካሁን በተሰጡ የሥልጠና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡ ሲሆን በሥልጠና ያገኛችሁትን ዕውቀት ወደ ተግባር መቀየር ከቻላችሁ ለውጥ ማምጣት ይቻላል ብለዋል።   የግብርናውን ዘርፍ መለወጥ ግድ እንደሚል ጠቁመው ኋላ ቀር የማረሻ ዘዴንና የአስተራረስ መንገድን በቴክኖሎጂ መቀየር እንደሚገባም ተናግረዋል። መሪዎች ለውጥ የሚያመጣ፣ እሴት የሚጨምር ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመው በግብርናው ዘርፍ ለውጥ ሲመጣ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማምጣት ቀዳሚው ጉዳይ ዘመናዊ ግብርናን መፍጠር አስፈላጊ ነው ብለዋል። ከፍጆታ አልፎ ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚኾንና ለውጭ ገበያ የሚያቀርቡ አርሶ አደሮችን መፍጠር እንደሚገባም አመላክተዋል። ሕልማችንን ማሳካት የሚያስችል ጸጋ አለን፣ መሬት፣ አየር፣ የማዕድን ሃብት፣ ትኩስ ጉልበት ያለው ወጣትና ሌሎች ሃብቶች አሉንም ብለዋል። ኢንዱስትሪን መለማመድ፣ የሚጠይቀውን አቅም በመጠቀም ውጤታማ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ከተሜነትንና የከተማ ዕድገትን በአግባቡ መምራት እንደሚያስፈልግም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።   ለቱሪዝም ዘርፉ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግ ጠቁመው አንዱ የምጣኔ ሃብት ማሳለጫ አድርጎ መሥራት እንደሚገባም አመላክተዋል። የቱሪዝም ሃብቶችን መለየት፣ መጠበቅ፣ ማልማትና ለጥቅም ማዋል እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎችን በውጤታማነት እንዲመሩና ለመስኖ ልማት፣ ለእንስሳት መኖ ዝግጅት ትኩረት እንዲሰጥም አሳስበዋል። የተፈጥሮ ሃብት ልማትን በተመለከተም ለማዕድን ሃብት ልማት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል። የንግድ ሥርዓቱን በተመለከተም ሕገ ወጥነትን፣ ኮንትሮባንድን መቆጣጠርና የገበያ ማዕከላትን መገንባት እንደሚገባ መግለጻቸውን አሚኮ ዘግቧል። የሰው ሃብት ልማታችን ላይ እንሥራ ያሉት አቶ አረጋ ከበደ የትምህርት ተቋማት መገንባት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። ማህበረሰቡ የጤና መድኅን ተጠቃሚ እንዲሆን በትኩረት እንዲሠሩና የሴቶችን፣ የወጣቶችን፣ የሕጻናትንና የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መሥራት እንደሚጠበቅም አመላክተዋል። አገልግሎት አሰጣጥ ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበው አገልጋዮች በጊዜ እና በቦታቸው ተገኝተው ለሕዝብ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡም አስገንዝበዋል። የሪፎርም ሥራን በውጤታማነት እንዲተገብሩና ስምንቱ ሪጂዮፖሊታን ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማስጀመርና ሌሎች ከተሞችም አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በቡድን-20 አባል አገሮች ጉባኤ ላይ ያደረገችው ተሳትፎ የላቀ ዲፕሎማሲ ስኬት የተመዘገበበት ነው
Nov 27, 2025 142
አዲስ አበባ፤ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በቡድን-20 አባል አገሮች ጉባኤ ላይ ያደረገችው ተሳትፎ የላቀ ዲፕሎማሲ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለጹ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ዋና ዋና የዲፕሎማሲ ስራዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው፥ ኢትዮጵያ የ2027 የኮፕ-32 (COP-32) ጉባዔን እንድታዘጋጅ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥን ለመግታት ለወሰደቻቸው እርምጃዎች እውቅና የሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ዓለም አቀፍ እውቅና እያገኘ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በኮሪደር ልማት፣ ንጹህ እና አረንጓዴ ከተሞችን ለማስፋፋት ለወሰደቻቸው ትላልቅ እርምጃዎች እውቅና የሰጠ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በስኬት ማስተናገዷ ለመመረጧ ሌላኛው ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የኮፕ-32 አስተናጋጅ ሆና መመረጧ በዲፕሎማሲው መድረክ ያላት ተሰሚነት ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል። ይህም የኢትዮጵያን በጎ ገጽታዎች ለማስተዋወቅና ለቱሪዝም ዕድገት ከፍተኛ ትርጉም ያለው መሆኑንም አስታውቀዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ-32) ተወካይ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የቡድን-20 ጉባኤ ላይ በመሳተፍ የዲፕሎማሲ ስኬት ማስመዝገቧን ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ባደረጉት ንግግር የአፍሪካን ሁነኛ አጀንዳዎችን ማንጸባረቃቸውንም አስታውሰዋል። ከበርካታ ሀገራትና የተለያዩ ተቋማት መሪዎች ጋር ስኬታማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቁመው፤ በዚህም የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል። በዚህም የልማት አጋርነት፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ጉዳዮችን ጨምሮ በበርካታ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን አንስተዋል። ይህም የኢትዮጵያ የላቀ የዲፕሎማሲ ከፍታ የተገለጸበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
ማህበራዊ
የባንዳነት ተልእኮ ተቀብሎ ለጥፋት የሚንቀሳቀሰውን ፅንፈኛ ቡድን በመታገል በኩል ሕዝቡ ከጸጥታ ሃይሉ ጋር እየሰራ ነው
Nov 28, 2025 47
ወልዲያ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የባንዳነት ተልእኮ ተቀብሎ ለጥፋት የሚንቀሳቀሰውን ፅንፈኛ ቡድን በመታገል በኩል ህዝቡ ከጸጥታ ሃይሉ ጋር በመሆን በጋራ እየሰራ መሆኑን በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ገለጸ። የሕዝብ ጠላትና የልማት ጸር በሆነው ጽንፈኛ ቡድን ላይ ሕግ የማስከበር ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አስተዳደሩ አስታውቋል። በአማራ ክልል በዞን፣ በወረዳ እና ከተሞች የተለያዩ የማሕበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰሞኑን ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በሰሜን ወሎ ዞንም የመንግስት ሰራተኞች፣ የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎችም ተመሳሳይ ውይይት ማድረጋቸው ይታወቃል። አጠቃላይ የነበረውን ውይይትና በተሳታፊዎች የተነሱ ሃሳቦች ምን ይመስላሉ፣ ምንስ ውጤት ተገኘባቸው በማለት ኢዜአ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አራጌ ይመርን አነጋግሯል። ዋና አስተዳዳሪውም በየመድረኮቹ ከሕዝቡ የተነሱ ነጥቦችና ጥቅል አስተያየቶች የፅንፈኛ ቡድኑን የጥፋት እንቅስቃሴ የሚያጋልጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ ዘረፋ፣ ግዲያ እና እገታ የሚፈፅመው ጽንፈኛ ቡድን የሕዝብ ጠላትና የልማት ጸር መሆኑን በተለያዩ ማሳያዎች ከየመድረኮቹ መነሳቱን አስታውሰዋል። በመሆኑም የባንዳነት ተልእኮ ተቀብሎ ለጥፋት የሚንቀሳቀሰውን ጽንፈኛ ቡድን ሕብረተሰቡ ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር እንደሚታገሉት ያረጋገጡበት መድረክ ነበር ብለዋል። የፅንፈኛ ቡድኑ ዓላማ ሕጻናት እንዳይማሩ፣ እናቶች በጤና ተቋም እንደይወልዱና አጠቃላይ በሕብረተሰቡ ዘንድ ሰላምና መረጋጋት እንዳይፈጠር መሆኑን በየመድረኮቹ በማንሳት በፅናት እንደሚታገሉት መናገራቸውን ገልጸዋል። ከጥፋት በመውጣት የመንግስትን የሰላም አማራጭ በመቀበል እድሉን መጠቀም እንደሚገባም በተደጋጋሚ ተነስቷል ብለዋል። አጠቃላይ ሕዝባዊ የውይይት መድረኮቹ የሰላምን አስፈላጊነት አጽንኦት በመስጠት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉበት ሁኔታ ላይ የጋራ አቋም የተያዘበት መሆኑን ገልጸዋል። በዚሕም የባንዳነት ተልእኮ ተቀብሎ ዘረፋ፣ እገታና ግድያ በሚፈፅመው ፅንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን አረጋግጠው፤ የሰላም አማራጭ የሚከተሉትንም ለመቀበል ዝግጁ ነን ብለዋል።
ጤናማ የአመጋገብ ስርዓት !
Nov 28, 2025 89
በጾምና ጾም በማይኖርበት ወቅት ያለ የአመጋገብ ሥርዓት በሰውነት ጤና ላይ የየራሱ ተጽዕኖ ስላለው በአግባቡ መደረግ እንዳለበት ይመከራል። ጾም በሳይንስ የተደገፉ ጥቅሞች እንዳሉት እና የጤና አንድ አጋር እየሆነ መምጣቱንም በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምግብ ሳይንስና ኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ለኢዜአ ተናግረዋል። በተጨማሪም ከበርካታ በሽታዎች እራስን በመጠበቅ ጤናማ ሕይወት ለመምራት እንደሚረዳ ታውቆ በስፋት የኑሮ ዘይቤ አካል እየሆነ ስለመምጣቱም አመላክተዋል። በጾም ወቅት ሰውነት እራሱን ያጸዳል፤ ይህም በብዙ መልኩ ጤናማ ሕይወት እንዲኖር ያስችላል ይላሉ። ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል ወይም በይበልጥ እንዳይወሳሰቡ ለማድረግ ጾም ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው በዘርፉ የተደረጉ ምርምሮች ማመላከታቸውንም አንስተዋል። በተለይም ክብደትን እና በሰውነት ውስጥ ያለ የስብ ክምችትን ለመቀነስ ብሎም ከፍተኛ ደም ግፊትን፣ እንዲሁም የስኳር መጠንን ለመቆጣጠር ጾም አንድ የሕይዎት ዘዬ እየሆነ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል በጾም ወቅት ሰውነት ስለሚደክም እና የሚፈልገው ፈሳሽ እጥረት ስለሚያጋጥም በቀላሉ የሚፈጩ እና ሰውነት የሚፈልገውን ፈሳሽ ማስገኘት የሚችሉ ምግቦችን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። በዚሁ መሠረት ከጾም በኋላ ምግብ በሚበላበት ሠዓት እንደ ጁስ፣ ሾርባ፣ አጥሚት፣ ሰሊጥ፣ ሱፍ፣ ተልባ፣ ኑግ፣ አትክልትና ፍራፍሬዎችን መጠቀም ተገቢ ነው ይላሉ። በተጨማሪም በፕሮቲን ይዘታቸው የበለጸጉ የጥራጥሬ ዓይነቶችን (ባቄላ፣ አተር፣ ምሥር) በደንብ በማብሰል መጠቀም እንደሚመከርም አንስተዋል። ጾም ከመፍታት በፊት (ከምግብ በፊት ውኃ መጠጣት) ድርቀት የነበረበትን የሰውነት ክፍል እርጥበት እንዲኖረውና ለተሳለጠ የምግብ መፈጨት ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት። በተቻለ መጠን ስብጥራቸው በርከት ያሉ የምግብ ዓይነቶችን መመገብ አንዱ የሌለው ንጥረ ነገር ከሌላኛው ስለሚገኝ በዚህ አግባብ መመገብ እንደሚመከርም አስረድተዋል።
ለመንግሥት ገቢ መሆን የነበረበትን ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ
Nov 27, 2025 302
አዲስ አበባ፤ ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ ለመንግሥት ገቢ መሆን የነበረበትን ከ100 ቢልዮን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፤ በቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶችና ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር በሚባሉ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተባባሪ ተቋማት ዙሪያ ጥናትና ክትትል ሲከናወን ቆይቷል፡፡ ፈቃድ ያላቸውና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በገቡት ውል መሰረት የማይሠሩ ፤ በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው የተሰረዘባቸው እንዲሁም ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው በስፖርት አወራራጅነት ተሰማርተው የነበሩ አካላት በዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ትስስር አማካይነት በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው የተገኙ ሲሆን፤ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም በኅብረተሰቡ ትብብር አማካኝነት 24 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መግለጫው አስታውቋል፡፡ በተለይ በሕጋዊነት ሽፋን ፈቃድ ያወጡት ድርጅቶች ላይ ክትትል ለማድረግ ሙከራ በተደረገበት ወቅት ሁሉም ፈቃድ ሲያወጡ ይዘውት ከነበረው ቢሮ መልቀቃቸውና አድራሻቸውን መሰወራቸው ተረጋግጧል፡፡ የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር ተብለው ከሚጠሩ የፋይናንስ ስርዓቶችን ከሚያሳልጡላቸው የሀገር ውስጥ የክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተቋማት ጋር በመመሳጠር በአጠቃላይ ሲያንቀሳቅሱት ከነበረው የገንዘብ መጠን መንግሥት በተለያዩ የገቢ አማራጮች ማግኘት የነበረበትን 100 ቢልዮን ብር በላይ መሰወራቸው እንደተደረሰበት አመልክቷል፡፡   የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ በተለያዩ የገንዘብ ክፍያ ስርዓቶች አማካይነት የሚሰበስቡትንና የሚያዘዋውሩትን የገንዘብ መጠን ያማከለ ግብር አለመክፈላቸው እንደተደረሰበት የጠቆመው መግለጫው፤ በክሪፕቶከረንሲ እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሃዋላ ገንዘብ ማስተላላፊያ አማራጮች አማካኝነት የሚያገኙትን ገቢ በውጭ ምንዛሪ በመቀየር ሲሰውሩና ከሀገር እንዲወጣ ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውቋል፡፡ ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር የሚባሉት የሀገር ውስጥ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተቋማቱ ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በመውሰድ የሚንቀሳቀሱ ቢሆንም፤ የደንበኛን ምስጢር መጠበቅ የሚል ሙያዊ አሠራርን እንደ ሽፋን ተጠቅመው የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች የሚያንቀሳቅሱትን የገንዘብ መጠን ከሚመለከታቸው የመንግሥት አስፈፃሚ ተቋማት በመደበቅ ወይም አሳንሶ በማቅረብ በግብር ስወራ እንዲሁም ከፍተኛ የሀገር ሀብትን ወደ ውጭ በማሸሽ ወንጀል ላይ ተሳትፎ እንዳላቸው የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መግለጫ አመልክቷል፡፡ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ግለሠቦች ጭምር ከኢትዮጵያ ውጪ ሆነው ሀገር ውስጥ ለሚገኙ ተባባሪዎቻችው ውክልና በመስጠት ሕገ-ወጥ ድርጊቱን ሲፈጸሙ መቆየታቸው እንዲሁም ውጭ ሀገር የበለጸጉ ሶፍትዌሮች ጥቅም ላይ መዋላቸውና ድርጅቶቹ ቋሚ አድራሻ የሌላቸው መሆኑ ወንጀሉን ውስብስብና ለቁጥጥር አስቸጋሪ አድርጎት ቢቆይም የደኅንነት ተቋሙ ከሌሎች የመረጃና የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ባደረጉት ስምሪት ተጠርጣሪዎቹ መያዛቸው ተመላክቷል፡፡ በሕገ ወጥ ድርጊቱ ከሀገር ሲሸሽ የነበረው ከፍተኛ ገንዘብ ሽብርተኝነትንና ጸረ ሰላም ቡድኖችን በገንዘብ ለመደገፍ፤ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ ለማስመሰል እንዲሁም ለኮንትሮባንድ ንግድ ማካሄጃ እንደሚውል የጠቆመው መግለጫው፤ ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በመጻረር የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅሞች ስጋት ላይ ለመጣል የሚደረግ እንቅስቃሴ አካል በመሆኑ ዜጎች ማንኛውም አይነት ተመሳሳይ እንቅስቃሴዎች ሲመለከቱ ለደኅንነትና ጸጥታ አካላት የሚሰጡትን ጥቆማ አጠናክረው እንዲቀጥሉ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ የላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡
ኢኮኖሚ
በምዕራብ ጎንደር ዞን ለበጋ መስኖ ልማት አስፈላጊ የግብርና ግብአቶች ቀርበዋል
Nov 28, 2025 12
ገንዳ ውኃ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ ለበጋ መስኖ ልማት የሚያስፈልጉ የግብርና ግብአቶችን በማቅረብ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን የሕብረት ሥራ ማህበራት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የመተማ ገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የአፈር ማዳበሪያ ለመስኖ ልማቱ እያቀረበ መሆኑም ተመሏክቷል። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ተወካይ ሲሳይ አለበል እንደገለጹት፣ ዞኑ ለመስኖ ልማት የሚውል ሰፊ መሬት፣ ለበጋ መስኖ ልማት የሚስማማ የአየር ንብረትና ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች ባለቤት ነው። በመሆኑም ይህን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ለበጋ መስኖ ልማት አስፈላጊ ግብአቶችን በማቅረብ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   በልማቱም የአርሶ አደሩን ዘላቂ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመረው የግብአት አቅርቦት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በመስኖ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች በየዓመቱ የግብዓት እጥረት ይገጥማቸው እንደነበር አስታውሰው፣ ዘንድሮ ችግሩን ለመፍታት በተደረገው ጥረት ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘር፣ ፀረ ተባይና ኬሚካል ቀድሞ መቅረቡን አቶ ሲሳይ ተናግረዋል። በመተማ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን የቀረበው ማዳበሪያም በበጋ መስኖ ልማት የሚሳተፉ አርሶ አደሮችን ምርታማነት በማሳደግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችል ነው። የመተማ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ ሥራ አስኪያጅ ሀብቴ ዘውዱ በበኩላቸው የበጋ መስኖ ልማትን በግብአት በመደገፍ ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ ነው። ለዚህም በተያዘው የበጋ ወቅት ለሚካሄደው የመስኖ ልማት ዩኒየኑ 2ሺህ 800 ኩንታል ዳፕ እና ዩሪያ ማዳበሪያ ማቅረቡን በማሳያነት ጠቅሰዋል። በገንዳውኃ ከተማ ዙሪያ በመስኖ ልማት የተሰማሩት አርሶ አደር አብዱ ሁሴን እንደገለጹት በልማቱ በየዓመቱ ይገጥማቸው የነበረው የማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት መፈታቱን ገልጸዋል።
ኮሌጁ የገጠሩን ማህበረሰብ ችግር ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ ነው 
Nov 28, 2025 15
ድሬደዋ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦የገጠሩን ማህበረሰብ ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት በተቀናጀ መንገድ እየሰራ መሆኑን በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ገለጸ። ኮሌጁ በታዳሽ ኃይል ልማት ከሚሰራ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በማህበር ለተደራጁ የገጠር ወጣቶች በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የእህል ወፍጮ አስረክቦ ወደ ስራ አስገብቷል። የኢትዮ -ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ወጣቱ የአካባቢውን ፀጋዎች አልምቶ እራሱንና አካባቢውን እንዲለውጥ በክህሎት የታገዘ የተለያዩ ስልጠናዎች ተዳራሽ እያደረገ ይገኛል።   በእስካሁኑ እንቅስቃሴ ለ120 ወጣቶች ክህሎት መር ስልጠና መስጠቱን ጠቅሰው በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የዘመናዊ ወፍጮ ባለቤት የተደረጉት የቃልቻ ገጠር ቀበሌ ወጣቶች የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከጀርመን ተራድኦ ድርጅት በተገኘ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የተገዛውንና በፀሐይ ሐይል የሚሰራ ወፍጮ በአይነትና በጥራት በኮሌጁ ሰርቶ ማሳያዎች (ወርክሾፖች) በማባዛት በገጠር ቀበሌዎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የገጠሩን ህብረተሰብ ማህበራዊ ችግሮች የሚፈቱትንና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ ወፍጮዎችን ለማባዛት በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ከሚሰሩ አጋር ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።   ከዚህ በተጨማሪ በገጠር ቀበሌዎች ለሚገኙ ወጣቶች የተለያዩ የክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት በፈጠራ እና በክህሎት ታግዘው የአካባቢያቸውን ሃብቶች ወደ ጥቅም እንዲለውጡ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በኤሌክትሪክ መሳሪያዎች መገጣጠምና መጠገን ስልጠና የተሰጣቸው በማህበር የተደራጁ ወጣቶች በበኩላቸው እንዳሉት፤ ኮሌጁ የገጠሩን ማህበረሰብ ችግሮችን ለመፍታት እያደረገ የሚገኘው ስራ የሚበረታታ ነው።   የማህበሩ አባል ወጣት ጀማል ኢብራሂም እንደተናገረው ፤ በፀሐይ ኃይል የሚሰራ ወፍጮ ከበቂ ስልጠና ጋር ማግኘታቸው ቀጣዩን የህይወቸውን ምዕራፍ ለመምራት ያስችላቸዋል። ይህን መሰል የተቀናጀ ድጋፍ ለወጣቶች ቢደረግ የወጣቱን ተስፋና ህይወት የበለጠ ለመለወጥ እንደሚያስችልም ነው የተናገረው።   የማህበሩ አባል ወይዘሮ ሩሚያ መሐመድ በበኩሏ፤ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰራው ወፍጮ 24 ሰአታት ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት የነበረውን ችግር ለመፍታት እንደሚያስችልም ገልጻለች ። እናቶች በውሃ እና በኤሌክትሪክ መቆራረጥ ምክንያት ይደርስባቸው የነበረውን ጫና ለመቀነስ ያግዛል ስትል ገልጻለች።
"ልወቅሽ ኢትዮጵያ" ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን እያጎለበተ ነው
Nov 28, 2025 28
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ "ልወቅሽ ኢትዮጵያ" የተሰኘው ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን በማነቃቃት በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የቱሪዝም ሚኒስቴር የፕሮሞሽን ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ተሾመ ተክሉ ለኢዜአ እንደገለጹት ልወቅሽ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ትውልዱ ስለ ሀገሩ ባህል፣ ታሪክ እና የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዲያውቅ ለማድረግ ያለመ ንቅናቄ ነው። ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በተለያዩ ከተሞች የ"ልወቅሽ ኢትዮጵያ" የሩጫ ውድድር ባለፉት ዓመታት እየተካሄደ እንደሚገኝ ለአብነት አንስተው ፕሮግራሙ በሀገር ውስጥ ቱሪዝም ላይ ትልቅ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። መርሃ ግብሩ ከሩጫው ባሻገር ልዩ የጉብኝት ፓኬጆችን በማዘጋጀት ዜጎች የተፈጥሮና የቅርስ ስፍራዎችን እንዲጎበኙ እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም በሩጫው ወቅት በሚያልፏባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ታሪካዊና ባህላዊ እሴቶችን እንዲገነዘቡ እያስቻለ መሆኑንም ጨምረው አስታውቀዋል። ውድድሩ በሚካሄድባቸው ከተሞች፣ የአካባቢው ማኅበረሰብ ከቱሪዝም ፍሰቱ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን ዕድል እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ከተሞቹ ልዩ ባህሪያቸውንና መስህቦቻቸውን ለብዙኀኑ በማስተዋወቅ የተሻለ ዕውቅና እያገኙ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ይህ የስፖርትና የቱሪዝም ትስስር የሀገር ውስጥ እንቅስቃሴን ከፍ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ ለሀገራዊ ብልጽግና የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ዳግም ተሾመ ፕሮግራሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ መምጣቱንና በአሁኑ ጊዜ በስድስት ከተሞች እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ ውድድሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲሁም የውጭ ዜጎች እየተሳተፉበት እንደሚገኙ አንስተው በርካታ ሰዎች በመርሃ ግብሩ ለማሳተፍ ፍላጎታቸውን እያሳዩ እንደሚገኙም አመልክተዋል፡፡ መርሀ ግብሩን በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞች ለማስፋት ዕቅድ መያዙንና ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በደንብ እንዲያውቁ የቱሪዝም ሀብቶችን እንዲጎበኙ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የዘንድሮው ልወቅሽ ኢትዮጵያ የሩጫ ውድድር ከጥር ጀምሮ በደብረብርሃን፣ ሀዋሳ፣ ጅማ፣ በቆጂ፣ አርባምንጭ፣ ሀረር ዲስከቨር ኢትዮጵያ ክላሲክ በሚል መሪ ቃል እንደሚካሄድ ተመላክቷል።
መስኖን ተጠቅመን ባለማነው አትክልትና ፍራፍሬ ተጠቃሚ ሆነናል-አርሶ አደሮች
Nov 28, 2025 45
ገንዳውኃ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ የበጋ መስኖን በመጠቀም ባለሙት አትክልትና ፍራፍሬ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን በልማቱ የተሳተፉ አርሶ አደሮች ገለጹ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ የነበራቸው አርሶ አደሮች እንደገለፁት፤ መስኖን በመጠቀም ባለሙት አትክልትና ፍራፍሬ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን አሳድገዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ ነዋሪው አርሶ አደር አደም ሁሴን ለኢዜአ እንደገለጹት መስኖን በመጠቀም ቋሚ አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ይገኛሉ።   ባለፉት ቅርብ ዓመታት ያለሙት የማንጎ፣ የፓፓያ፣ የዘይቱን፣ የሙዝ፣ የሎሚና የሌሎች የፍራፍሬ ዝርያዎች ምርት መስጠት በመጀመራቸው ባለፈው ዓመት ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮ ዓመትም ካለፈው የተሻለ ገቢ ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ጠቁመው ከሚያገኙት ገቢም በባንክ በመቆጠብ በቀጣይ ወደ ተሻለ ኢንቨስትመንት ለመግባት ፍላጎቱ እንዳላቸውም አስረድተዋል። ሌላኛው የዚሁ ከተማ ነዋሪ አርሶ አደር ሙሀመድ ገደፋው በበኩላቸው፤ የፍራፍሬ ልማት በቅርብ ጊዜ የተጀመረ ቢሆንም የሚሰጠውን ጥቅም በመረዳት በብዛት የማልማት ስራ እየሰራሁ ነው ብለዋል።   በሩብ ሄክታር ማሳቸው ላይ ባለሙት ፍራፍሬ በዓመት ከ150 ሺህ ብር በላይ ገቢ እያገኙ መሆኑን ጠቁመው የፍራፍሬ ልማቱን ወደ አንድ ሄክታር ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል። ቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት አዋጭ መሆኑን በመገንዘብ አንድ ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ በዘርፉ መሰማራቱን የገለፀው ደግሞ የመተማ ዮሃንስ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት ሰውበሰው አለነ ነው።   ከሁለት ሄክታር በላይ መሬት ላይ ያለማው የማንጎ፣ የፓፓያ፣ የሎሚ፣ የብርቱካንና የዘይቱን ተክል ምርት መስጠት በመጀመሩ እስካሁን ያወጣውን ወጪ በዘንድሮው የምርት ሽያጭ እንደሚመልስም ተስፋ አድርጓል። በምእራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ባለሙያ አቶ አስናቀው አራጋው እንዳሉት፤ በዞኑ አንድ ሺህ 200 ሄክታር መሬት በፍራፍሬና ቋሚ አትክልት ለምቷል። በዚህም 35 አርሶ አደሮችንና ባለሃብቶችን በማሳተፍ በተካሄደው የፍራፍሬ ልማት ባለፈው ዓመት ከ170 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።   በተያዘው በጀት ዓመትም ከ200 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ አስረድተዋል። እየተገኘ ያለውን ጥቅም በቀጣይ ለማስፋትም ዘንድሮ ከ250 ሺህ በላይ አዳዲስና ቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል ፍል የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በተጨማሪም በዞኑ የሚካሄደው የፍራፍሬ ልማት ለወጣቱ የስራ እድል መፍጠሪያ ዋና አማራጭ ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ አመልክተዋል። አርሶ አደሮች የሚፈልጉትን የፍራፍሬ ችግኝ በቀበሌና በወረዳ ማዕከላት ለማሰራጨት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ምሕዳሩን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 
Nov 27, 2025 151
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ምሕዳሩን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አስታወቁ። "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ሲካሄድ የቆየው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል። ተቀማጭነቱን አሜሪካን ሀገር ያደረገው ግሎባል ኢንተርፕርነርሺፕ ኔትወርክ፤ ኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ ባዘጋጀቻቸው ኹነቶች ከ200 ሀገራት ጋር ተወዳድራ አንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጿል።   የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢንተርፕርነር ምህዳር ግንባታ ላይ የተከናወኑ ስራዎች በዘርፉ ውጤት እንዲመዘገብ አድርጓል። በአሁኑ ወቅት በኢንተርፕርነር ዘርፉ ላይ የተገኘው ስኬት የኢትዮጵያን አዲስ መልክና እድገት ለማስተዋወቅ የሚረዱ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ውድድር በማድረግ ከዓለም ስምንተኛ ከአፍሪካ ደግሞ ሁለተኛ በመሆን አጠናቅቃ እንደነበርም አስታውሰዋል። በዘንድሮው ዓመትም በርካታ ተቋማት በመደመር እሳቤ በዘርፉ በትብብር መስራታቸው ኢትዮጵያ ቀዳሚውን ስፍራ በመያዝ ውድድሩን እንድታጠናቅቅ አድርጓል ነው ያሉት።   በአጭር ጊዜ ውስጥ የኢንተርፕርነር ዘርፍ ምህዳርን በማስፋት ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ ተችሏል ያሉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ፤ በቅንጅት ከተሰራ የኢትዮጵያን እድገት ለማሳካት እንደማያዳግትም አመላካች መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በውድድሩ ያስመዘገበችው ውጤት ኢንቨስትመንትን ከመሳብ ባሻገር ችግር ፈቺ ኢንተርፕርነሮችን እና በዘርፉ ምርምር የሚያደርጉ አካላትን ለማፍራት እንደሚረዳ አብራርተዋል፤ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሀሰን ሁሴን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በዘንድሮው ዓመት ኢንተርፕነር ዘርፉን ለመለወጥ በጋራ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል። ይህንን ጥረት በማጠናከርም በቀጣይ በተለይ የዘርፉን ምህዳር የማስፋት ስራን ስኬታማ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውም ነው ጥሪያቸውን ያስተላለፉት ።
ኢትዮ ቴሌኮም ሶስተኛውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት አስጀመረ
Nov 27, 2025 139
አዲስ አበባ፤ ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም ሶስተኛውንና እጅግ ፈጣን የሆነውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት በአዲስ አበባ አስጀምሯል። ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ሰሚት በተለምዶ ፍየል ቤት አካባቢ ያስገነባውን ሶሰተኛውን ዘመናዊና ፈጣን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት የኢት ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ እንዳሉት ጣቢያው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መጠቀምን የሚያበረታታና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የተጀመረው ጥረት አንዱ አካል ነው።   ኢትዮ ቴሌኮም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ከማድረግ በተጨማሪ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን ገልፀው፤ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ መሙያ ጣቢያ ግንባታ የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የባትሪ መሙያ ጣቢያው የተገጠመለት ቴክኖሎጂ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና አስተማማኝ መሆኑን ጠቁመዋል። እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) ቴክኖሎጂ የባትሪ መስፈርቶችን በመተንተን እንዲሁም የባትሪውን ደህንነት በመፈተሽ የተሽከርካሪውን ባትሪ በፍጥነት ቻርጅ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል። ከዚህ በፊት ተቋሙ በተከላቸው ሁለት የባትሪ መሙያ ማዕከላት ከ165 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች የኤሌክትሪክ ቻርጅ መጠቀማቸውን ጠቁመዋል። ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያው በአንድ ጊዜ 16 ተሽከርካሪዎች ባትሪ እንዲሞሉ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው፤ አንድ መኪና በ15 ደቂቃ ባትሪውን መሙላት እንደሚችል ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ በአራተኛ መደበኛ ስብሰባው እንዲፈፀሙ ያስቀመጣቸውን ተግባራት አፈፃፀም በጥልቀት በመገምገም አቅጣጫ አስቀምጧል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ተመስገን ጥሩነህ
Nov 26, 2025 595
የብሔራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት በአራተኛ መደበኛ ስብሰባው እንዲፈፀሙ ያስቀመጣቸውን ተግባራት አፈፃፀም በጥልቀት በመገምገም አቅጣጫ ማስቀመጡን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የብሔራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት በዛሬው ዕለት አምስተኛ መደበኛ ስብሰባውን ማካሄዱን አስታውቀዋል። ምክር ቤቱ በአራተኛ መደበኛ ስብሰባው እንዲፈፀሙ ያስቀመጣቸውን ተግባራት አፈፃፀም በጥልቀት በመገምግሞ አቅጣጫ አስቀምጧል ነው ያሉት። ምክር ቤቱ አጠቃላይ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የስራ ክንውን፣ የዲጂታል መታወቂያ የምዝገባ ሂደት እንዲሁም ‘የ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደርስ’ ኢኒሼቲቭ ትግበራ አፈጻጸምን ገምግሞ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ደርሷል ሲሉም ገልጸዋል፡፡   ከዚህም በተጨማሪ በአገራችን በመከናወን ላይ የሚገኙ እንዲሁም አዳዲስ የዲጂታል ሰራዎች ከዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ጋር ያላቸውን ተጣጣሚነትን በውይይታችን ዳሰናል ብለዋል። በመጨረሻም ምክር ቤቱ ረቂቅ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ላይ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኃላ ስትራቴጂ ሰነዱን በማፅደቅ ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል ነው ያሉት። የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታችን በእመርታ የሚያድግበት ዘመን ላይ እንደመሆኑ፤ ምክር ቤቱም ለዚሁ ዕድገት ተገቢውን ሚና ለመወጣት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አስታውቀዋል፡፡
በመናኸሪያው የተጀመረው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት እንግልትን አስቀርቷል
Nov 26, 2025 120
ሆሳዕና፤ ህዳር 17/2018(ኢዜአ)፦ በሆሳዕና ከተማ በህዝብ መናኸሪያ የተጀመረው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በተሳፋሪ ላይ ሲደርስ የነበረን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪና እንግልት ማስቀረቱን ተገልጋዮች ገለጹ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በበኩሉ ለህዝብ የሚሰጠው የትራንስፖርት አገልግሎት ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። መንግስት የትራንስፖርት ዘርፉን ማነቆዎች በመፍታት በህዝቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስና የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።   በዚህም በዲጂታል የታገዘ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት በህዝብ መናኸሪያዎች የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በማስጀመሩ ለውጥ እየተመዘገበ መጥቷል። ኢዜአ በሆሳዕና ከተማ የህዝብ መናኸሪያ ተገኝቶ ያነጋገራቸው ተሳፋሪዎችና አሽከርካሪዎች በመናኸሪያው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ትርፍ ሰው ከመጫንና ተጨማሪ ክፍያን በማስቀረት በተሳፋሪ ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት ማስቀረቱን ተናግረዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ወንድም ዳኜ እንደገለጹት ፤ ከዚህ ቀደም በመናኸሪያው ትርፍ መጫንና ማስከፈልን ጨምሮ የተለያዩ እንግልቶች ይገጥሙ ነበር።   በዲጂታል የተደገፈ አገልግሎት መስጠት ከተጀመረ ወዲህ ከትራንስፖርት አገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ቀደም ሲል ሲገጥሙን የነበሩ ችግሮች ተፈተዋል፤ አሰራሩም በቀጣይ መጠናከር አለበት ብለዋል። አቶ አየለ ጊፊሶ የተባሉ ተሳፋሪ በበኩላቸው እንዳሉት በመናኸሪያው የተጀመረው የኢ-ትኬቲንግ አገልግሎት ተገቢ ያልሆነ ክፍያን ከማስቀረት ባለፈ በተሳፋሪ ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት አስቀርቷል።   ይሁንና የዲጂታል አገልግሎቱ በወረዳ ባሉ መናኸሪያዎች ባለመጀመሩ ከታሪፍ ውጭ ማስከፈል አሁንም እንዳለ ጠቅሰው ዲጂታል ትራንስፖርት አገልግሎቱ በሁሉም መዋቅሮች እንዲስፋፋ ጠይቀዋል፡፡ መንግስት ባስቀመጠው የታሪፍ ክፍያ መሰረት ማህበረሰቡን እያገለገሉ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በመናኸሪው የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪው ግዛቸው ሃይሉ ናቸው።   የኢ-ቲኬቲንግ መጀመር ከተራ አስከባሪዎች ጋር የነበራቸውን ያለመግባባት ችግር መፍታቱን ተናግረዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በክልሉ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎትን ዲጂታላይዝ በማድረግ የተመዘገበውን ውጤት ለማጠናከር ይሰራል ብለዋል።   የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በክልሉ በሚገኙ 23 መናኸሪያዎች ተግባራዊ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ አገልግሎቱ በትራንስፖርት ዘርፍ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን ከመቀነስ አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰው፣ በቀጣይም አገልግሎቱን በሁሉም መናኸሪያዎች የማስፋት ሥራ ይሰራል ብለዋል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል 
Nov 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከረፋዱ 4 ሰዓት ላይ ሃዋሳ ከተማ ከሲዳማ ቡና በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ካደረጋቸው ስምንት ጨዋታዎች መካከል ስድስቱን ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። 16 ግቦችን በጨዋታዎቹ ላይ ሲያስቆጥር ሰባት ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ18 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና በበኩሉ በውድድር ዓመቱ ሰባት ጨዋታዎችን አድርጎ ሁለት ጊዜ ድል ሲቀናው በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። ሶስት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥቷል። ሰባት ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ አምስት ግቦች ተቆጥረውበታል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ሲዳማ ቡና በዘጠኝ ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሃ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከይርጋጨፌ ቡና ከቀኑ 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ ባካሄዳቸው ስምንት ጨዋታዎች ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ አምስት ጊዜ ተሸንፏል። ስምንት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 13 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በዘጠኝ ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። አዲስ አዳጊው ይርጋጨፌ ቡና በበኩሉ ከሰባት የሊጉ ጨዋታዎች መካከል ሁለቱን ሲያሸንፍ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ሽንፈትን አስተናግዷል። በአራት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ ሶስት ግቦች ሲያስቆጥር ስድስት ግቦችን አስተናግዷል። ይርጋጨፌ ቡና በ10 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።   የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት መርሃ ግብር እስከ ሕዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ24 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ባህር ዳር ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ 13ኛ እና 14ኛ ደረጃን ይዘው ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛሉ። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን የኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰለሞን በ16 ግቦች ትመራለች። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ መሳይ ተመስገን በአምስት ግቦች ትከተላለች።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመቀሌ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና ከአርባምንጭ ከተማ ያደረጓቸው ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ
Nov 27, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 18/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ስምንተኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ተካሄደዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ መቀሌ 70 እንደርታ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ኪቲካ ጅማ እና ሱሌይማን ሀሚድ ለመቀሌ 70 እንደርታ ግቦቹን አስቆጥረዋል። አዲስ ግደይ እና ኤፍሬም ሌጋሞ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጎሎቹን ከመረብ ላይ ያሳረፉ ተጫዋቾች ናቸው።   መቀሌ 70 እንደርታ በሶስት ነጥብ 19ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ እስከ አሁን በሊጉ ምንም ጨዋታ አላሸነፈም። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ10 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕና ከአርባምንጭ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። እዮብ አለማየሁ ለሀዲያ ሆሳዕና እና ታምራት እያሱ ለአርባምንጭ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሀድያ ሆሳዕና በሰባት ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።   አርባምንጭ ከተማ በአራት ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ በውድድር ዓመቱ አንድም ጨዋታ ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ የሊጉ ጨዋታ ምድረገነት ሽሬ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የሰባተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የስምንተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከሕዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለተተከሉ ችግኞች በተደረገ እንክብካቤ የጽድቀት መጠንን ማሳደግ ተችሏል
Nov 28, 2025 23
ደብረ ማርቆስ ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ለተተከለው ችግኝ የእንክብካቤ ስራ እየተካሄደ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የተፈጥሮ ሃብት ቡድን መሪ አቶ ንጉሴ ሽመልስ ለኢዜአ እንደገለጹት የሚተከሉ ችግኞችን የጽድቀት መጠን በመጨመር የደን ሽፋኑን ለማሳደግ የእንክብካቤ ስራ እየተሰራ ነው።   በዚህም ባሳለፍነው ክረምት ከተተከለው ከ219 ሚሊዮን በላይ ችግኝ ውስጥ 87 በመቶ የሚሆነው መጽደቅ መቻሉን ገልጸዋል። በዚህ ዓመት የተመዘገበው የችግኝ ጽድቀት መጠን ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከሰባት በመቶ በላይ ብልጫ እንዳለው ተመልክቷል። ከ500 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ችግኞችን በማረም፣ በመኮትኮት፣ ውሃ በማጠጣትና ከእንስሳት ንክኪ ነጻ በማድረግ በተሰራው ስራ የጽድቀት መጠኑ እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል። በዞኑ የአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ ነዋሪ አቶ መንግስቱ ስሜነህ እንዳሉት፤ በአረንጓዴ ልማቱ የተተከሉ ችግኞች የመሬታቸውን ለምነት በመጨመር ምርታማነታቸው እንዲያድግ እያደረገ ነው። ይሄን በመገንዘብም ዘንድሮ የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ ለማድረግ በመጠበቅና በመንከባከብ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።   የደጀን ወረዳ የሽንቡሪ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አንዷለም አምሳሉ በበኩላቸው ፤ በየዓመቱ የሚተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የጽድቀት መጠኑ እንዲጨምር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የተተከሉ ችግኞች የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ ማድረጋቸውን ጠቁመው በቀጣይም ችግኞችን የመትከልና የመንከባከብ ስራን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ የተሰሩ ተግባራት የዞኑን የደን ሽፋን ባለፈው ዓመት ከነበረበት ከ17 ነጥብ 4 በመቶ ወደ 18 ነጥብ 1 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤን እንድታዘጋጅ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ለሰራቻቸው ውጤታማ ሥራዎች የተሰጠ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ነው 
Nov 27, 2025 110
አዲስ አበባ፤ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤን እንድታዘጋጅ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ለሰራቻቸው ውጤታማ ሥራዎች ዳግም የተሰጠ ዓለም አቀፍ ዕውቅና መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ዋና ዋና የዲፕሎማሲ ስራዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ ጉባኤውን እንድታዘጋጅ መመረጧ በአረንጓዴ ልማት፣ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ማበረታቻ፣ በአረንጓዴ ዐሻራ እና መሰል የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራዎች ላይ እያከናወነች ለሚገኙ ተግባራት የተሰጠ እውቅና ነው። ኢትዮጵያ የኮፕ-32 አስተናጋጅ ሆና መመረጧ በዲፕሎማሲው መድረክ ያላት ተሰሚነት ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ-32) ተወካይ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውንም ተናግረዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ አጀንዳዎቿን ለዓለም የምታስተዋውቅበት ትልቅ መድረክ እንደሚሆንም አምባሳደሩ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የቡድን-20 ጉባኤ ላይ በመሳተፍ የዲፕሎማሲ ስኬት ማስመዝገቧን ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ባደረጉት ንግግር የአፍሪካን ሁነኛ አጀንዳዎችን ማንጸባረቃቸውንም አስታውሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከተመድ፣ ከዓለም ባንክ፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክ፣ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) እና ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች ጋር ውጤታማ የጎንዮሽ ውይይቶችን ማድረጋቸውንና በርካታ ስምምነቶች መፈጸማቸውን ገልጸዋል። የማሌዥያና የሲንጋፖር ሀገራት መሪዎች የሥራ ጉብኝት ኢትዮጵያ ካላት ሁለገብ የልማት ጉዞ አንፃር ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከሀገራቱ ጋር በነዳጅ፣ በታዳሽ ኃይል፣ በግብርና፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በስማርት ከተማ ልማት እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ስምምነት መደረጉን አስታውቀዋል። በተሰሩ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራዎች ምክንያት የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲያቸውን በአዲስ አበባ የከፈቱ ሲሆን፣ ሌሎችም ለመክፈት መወሰናቸው በመግለጫው ተመላክቷል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ መስክ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተም፤ በሳውዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ወደ 23 ሺህ የሚጠጉ ዜጎችን በቅርቡ ወደ ሀገር መመለስ እንደተቻለ ተመላክቷል። ኢትዮጵያ በብራዚል ቤለም በተካሄደው የዓለም የአየር ንብረት (COP-30) ጉባኤ ላይ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት (COP-32) ጉባኤ ለማስተናገድ መመረጧ ይታወቃል።  
መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉና ለዱር እንስሳት ሀብት የሰጠው ትኩረት ለዱር እንስሳት ጥበቃ ምቹ መደላድል ፈጥሯል
Nov 27, 2025 101
አዲስ አበባ፤ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉና ለዱር እንስሳት ሀብት የሰጠው ትኩረት ለዱር እንስሳት ጥበቃና ባለስልጣኑ ለሚያከናውነው ተግባር ምቹ መደላድል መፍጠሩን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ ገለፁ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ በትናንትናው እለት በለንደን በተካሄደው በአፍሪካ በብዝሃ ህይወት ጥበቃ የሚሰጠው ፕሪንስ ዊሊያም አዋርድ የ2025 አሸናፊ ሆነዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አሸናፊ የሆኑት ተስክ ጥበቃ ሽልማት 2025 በተዘጋጀው በአፍሪካ በብዝሃ ህይወት ጥበቃ የላቀ ድርሻና አስተዋፅኦ ላበረከቱ ሰዎች በሚሰጠው የህይወት ዘመን አበርክቶ ሽልማት ዘርፍ ነው። አቶ ኩመራ በዱር እንስሳት ጥበቃ ዘርፍ ከባለሙያነት እስከ ዋና ዳይሬክተርነት ከ30 ዓመት በላይ ያገለገሉ ሲሆን በዘርፉ በተለያዩ የጥናት እና ምርምር እንዲሁም የአስተዳደር ሥራዎች ላይ ያበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ ሽልማቱን ለማሸነፍ አስችሏቸዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ እንዳሉት ባለስልጣኑ የዱር እንስሳትና መኖሪያ አካባቢያቸው በአግባቡ ተጠብቆና ለምቶ በዘላቂነት ጥቅም ላይ ለማዋል እየሰራ ይገኛል። የጥበቃ ቦታዎችን በጥናት ለይቶ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ማቋቋም እንዲሁም የአስተዳደር ስርዓት ዘርግቶ በአግባቡ እንዲጠበቁና እንዲለሙ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ባለስልጣኑ የዱር እንስሳት መጠለያ፣ የስፖርታዊ አደን የሚካሄድባቸው ጥበቃ ቦታዎችን ጨምሮ በተለያዩ ምድብ ያሉ የጥበቃ ቦታዎች በአግባቡ እንዲጠበቁ የማድረግ ስራም ያከናውናል ነው ያሉት። የጥበቃ ስራዎችን ከክልሎች፣ከማህበረሰቡ የሚመለከታቸው አካላት ጋር ከመስራት ባለፈ በዱር እንስሳት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል ከአገራት ጋር በመተባበር እንደሚሰራም ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉና ለዱር እንስሳት ሀብት የሰጠው ትኩረት ለዱር እንስሳት ጥበቃና ባለስልጣኑ ለሚያከናውነው ተግባር ምቹ መደላድል መፍጠሩን ጠቁመዋል። ያገኙት ሽልማትም ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት አለም አቀፍ እይታ እንዲያገኝ ለማስቻሉ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ሽልማቱ ለዱር እንስሳት ጥበቃ የበለጠ ድምፅ ለመሆን፣ ህፃናት ለተፈጥሮ ሀብት ያላቸውን ተቆርቋሪነት ለማሳደግና የተፈጥሮ ሀብት አርበኛ የሆኑት ሬንጀሮች ማህበር የበለጠ ለማጠናከር እንዲተጉ የቤት ስራ የሚሰጥ ነው ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 375
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 326
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ለሱዳን ግጭት ዓለም አቀፍ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል- ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Nov 19, 2025 433
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የሱዳን ግጭት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቀናጀ ምላሽ እንዲሰጥ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ያዘጋጀው ሁለተኛ የሱዳን የልዩ ልዑኮች ፎረም ዛሬ በጅቡቲ ተካሄዷል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ተዋንያን ተሳትፈዋል። ፎረሙ በሱዳን ላለው ቀውስ የተቀናጀ መልስ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።   የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የሱዳን ሰላም በሱዳናውያን የሚመራ፣ ቀጣናዊ ትብብር የተረጋገጠበት እና ዓለም በአንድ ድምጽ የሚደግፈው ሊሆን እንደሚገባ አመልክተዋል። በሱዳን ያለውን ግጭት ለማስቆም፣ ንጹሃን ዜጎችን ለመጠበቅ እና የኢጋድ ቀጣናን የተረጋጋ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን በሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ የሰብዓዊ እርዳታ መተላለፊያ እንዲከፈት እና ተአማኒነት ያለው የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። ኢጋድ ሱዳናውያን በሀገራቸው ሰላም እና ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ክብራቸው እንዲጠበቅ ያላቸው መሻት እንዲሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በመረጃው አመልክቷል።
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 734
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 503
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 536
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 599
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 758
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2446
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2549
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3444
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3528
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 1705
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1140
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6959
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5439
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57172
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52242
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32940
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30452
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26507
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25211
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24811
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24796
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57172
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52242
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32940
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30452
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ድንበር ተሻጋሪው የኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር ወዳጅነት
Nov 27, 2025 125
ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1969 ነው። ሀገራቱ በተለያዩ ክፍለ አህጉራት የሚገኙ ቢሆንም ርቀት ሳይገድባቸው በዲፕሎሲ እና ኢኮኖሚ መስኮች ያላቸውን ትብብር ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ለማስፋት እየሰሩም ይገኛሉ። ሲንጋፖር በፍጥነት እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፣ ስትራቴጂካዊ ስፍራና ከፍተኛ የህዝብ ብዛት በመጠቀም ትስስሯን የማጎልበት ጠንካራ ፍላጎት አሳይታለች። እ.አ.አ በ2017 የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና የሲንጋፖር የሕብረት ስራ ኢንተርፕራይዝ የተፈራረሙት የጋራ መግባቢያ ስምምነት የዚሁ ማሳያ ነው። ስምምነቱ ሲንጋፖር በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማትና የንግድ ስራ ምቹነት ሪፎርሞች ልምዷን የምታካፍልበት ነው። ሎጅስቲክስ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማዕድንና ቱሪዝም ትብብራቸውን ለማጠናከር የጋራ ስምምነት ላይ ከደረሱባቸው መስኮች መከላከል ይጠቀሳሉ። ኢትዮጵያ ለሲንጋፖር የአፍሪካ የኢንቨስትመንት መግቢያ በር፣ ሲንጋፖር ለኢትዮጵያ የእስያ መግቢያ በር ናቸው ማለት ይቻላል። ሁለቱ ሀገራት በተደጋጋሚ የንግድ እና ኢንቨስትመንትን ጨምሮ አጠቃላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛው የሀገራቱ የትብብር መስክ አቪዬሽን ነው። የኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር አየር መንገዶች እ.አ.አ በ2012 የአየር አገልግሎት ትብብር ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። ስምምነቱ የመንገደኞችና ካርጎ በረራዎችን እንዲሁም የትራንስፖርት ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችል ነው። የአየር አገልግሎት ስምምነቱ በምስራቅ አፍሪካና በደቡብ ምስራቅ እስያ መካከል በጉዞ፣ በካርጎ ንግድ እና ሎጅስቲክስ ያለውን ትብብር ለማጎልበት ያስችላል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እ.አ.አ በ2024 በሲንጋፖር ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል። ጉብኝቱ ሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩበት 55ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር የተገጣጠመ ነበር። በጉብኝቱ ወቅት ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ሀገራቱ በመደበኛነት የሁለትዮሽ ምክክር እንዲያደርጉ፣ በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ነው። ሲንጋፖር በኢትዮጵያ ኤምባሲ እንደምትከፍት ይፋ አድርጋለች። የሲንጋፖር ውሳኔ ከኢትዮጵያ አልፎም ከቀጣናው ጋር በትብብር ለመስራት ያላትን የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሆኗል።   የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ በቅርቡ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን ትብብራቸው ዙሪያ መክረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ውይይቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል ያለውን ግንኙነት ለጋራ ነጋችን ወሳኝ በሆኑ መስኮች በጋራ ለመሥራት በምናደርገው ጥረት ውስጥ አንድ ጠቃሚ ርምጃ ነው ሲሉም ገልጸውታል። በተለይም በክሂሎት ልማት እና የካርበን ብድር ትብብር ላይ የተፈረሙት የመግባቢያ ስምምነቶች ጽኑ እና ለነገው ገበያ ዝግጁ የሆኑ ሠራተኞችን ለማፍራት ብሎም በአየር ንብረት ጥበቃ ረገድ ዘላቂ፣ ዝቅተኛ ካርበን የሚያወጣ እድገት ለማረጋገጥ ያለንን የጋራ አቋም ያንጸባርቃል ነው ያሉት። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም በላቀ ተግባራዊ ትብብር ንግድ እና ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት፣ ዘመናዊ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስን በማልማት፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በገንዘብ ልውውጥ ቴክኖሎጂ፣ ሳይበር ደኅንነትና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለንን ትብብር ለመጠቀም እጅግ ሰፊ አቅም አለ ነው ያሉት። ሁለቱም መሪዎች በጉብኝቱ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማላቅ፣ ተቋማዊ መስተጋብርን ለማጠናክር ብሎም የወል ቅድሚያዎቻቸውን ከፍ አድርጎ ለመከወን መንገዶችን እንደተመለከቱበትም ተናግረዋል። ሲንጋፖር በኢትዮጵያ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗ ከኢትዮጵያ ባለፈ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትስስር ማጎልበት የሚያስችላትን ማዕቀፍ እንደሚፈጥር የገለጹት ደግሞ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ ናቸው። ከዚህ በፊት የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ኢትዮጵያን የጎበኙት እ.አ.አ በ1964 እንደነበር አስታውሰው የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከር እና ለሲንጋፖር አዳዲስ የንግድ በሮች መክፈት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል። አስተዳደር፣ ትምህርት እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ከሚፈልጉባቸው መስኮች መካከል እንደሚጠቀሱ አንስተው የሀገራቱ መሪዎቹ በተገኙበት ከቁልፍ የጋራ ፍላጎቶቻችን ጋር የሚጣጣሙ የክህሎቶች ልማትና የካርቦን ገበያ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራረመናል ብለዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት ተናግረዋል። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖር እና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድል በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር የቅርብ ጊዜ ውይይቶችና የጉብኝት ልውውጦች ሀገራቱ በጋራ ለመልማትና ለማደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት ትብብር በአፍሪካ እና በደቡብ ምስራቅ እስያ መካከል እንደ ድልድይ ሆኖ የሚያገለግል ነው።
በጥምር ግብርና ስኬት ያስመዘገቡት አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ
Nov 14, 2025 612
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ - ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ጨዛ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ለዘመናት ባከናወኑት የግብርና ልማት ሥራ ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ የዘለለ አልነበረም። ዛሬ ላይ ሆነው ያን ዘመንና ያሳለፉትን ዕድሜ ሲያስታውሱ ይቆጫሉ። በኋላ ቀር መንገድ ሲያከናውኑት ከነበረው የግብርና ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆንም፤ ሀብት ማፍራትም ሳይችሉ ቀርተዋል።   አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ይባላሉ። ከሰበሰቡት ሰብል ጎተራቸው ሳይጎድል፣ ከእንስሳት እርባታ ስራቸውም ጥገታቸው ሳትነጥፍ ማየት የዘውትር ህልማቸው ነበር። ለም መሬት ይዘው ምርታማ ባለመሆናቸው ሲቸገሩ፣ የሚሰራ ጉልበት ይዘው ማዕዳቸው እየጎደለ የጎልማሳነት ዕድሜ መባቻ ድረስ ችግር ሲፈራረቅባቸው ዓመታትን አሳልፈዋል። ይህ ፍላጎታቸው ሰምሮ፣ ጓሯቸው ለምቶ፣ ቤታቸው ሞልቶና ጥሪት አፍርተው የማየት ውጥናቸው ሳይሳካ ዓመታት ቢቆጠሩም ዛሬ ግን በጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ነገሮች ተቀይረዋል። የዓመታት ምኞታቸውን ማሳካት ጀምረዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ለስኬት እንዲበቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢያቸው አርአያ የሆኑ አርሶ አደር አድርጓቸዋል። የጥምር ግብርና ስራቸው ለዓመታት ከነበሩበት ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ በማውጣት ለአፍም ለኪስም ሆኗቸዋል። የመንግስት የልማት ትኩረት የሆነው ጥምር ግብርና በውስን መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅንጅት እንዲያለሙ እድል ፍጥሮላቸዋል። በዋናነት በሰብል፣ በእንሰት፣ በፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ላይ አተኩረው እየሰሩ ይገኛሉ። ይህም የአንዱ ክፍተት በሌላው እየተሞለ ውጤታማ ስላደረጋቸው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው። ለቤት ፍጆታ ብቻ ያመርቱ የነበረው የእንሰት ምርትን በማስፋፋት ችግኙንና ተረፈ ምርቱን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጭምር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያመርቱት ገብስ ለሌሎች አርሶ አደሮች ምሳሌ መሆን ችለዋል።   ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ስለሚያረቡም ወተት ከማጀታቸው አይጠፋም። በጓሯቸው የሚያለሙትን አትክልትና ፍራፍሬ ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል። አርሶ አደሩ ከንብ ማነብ ሥራቸውም እንዲሁ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው። ከአካባቢው ስነምህዳር ምክንያት ብዙም ያልተለመደውን ቡና በመትከል ለፍሬ አብቅተዋል። የእሳቸውን ፈለግ የተከተሉ ሌሎች አርሶ አደሮችም ቡና ማልማት ጀምረዋል። በእጅ ያለን ሀብት ወደ ውጤት ለመቀየር ተግቶ መስራትና ጽናት ያስፈለጋል ያሉት አርሶ አደር ወልዴ፣ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ሙያዊ ድጋፍና የተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ለውጤታቸው ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የእርሻ ልማትና የእንስሳት እርባታውን በቅንጅት ማከናወናቸውም እንዲሁ። አርሶ አደር ወልዴ የዓመታት ቁጭታቸው ዛሬ መፍትሄ እያገኘ ነው። የጥምር ግብርና ሥራቸው በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉና ልጆቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል። መኖሪያ ቤትን ጨምሮ የተለያየ ሀብት ለማፍራት ምክንያት በመሆኑም ልማቱን አስፋፍቶ ለማከናወን አቅደዋል።   አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጭምር አርአያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙራዱ ብሩ ናቸው። ቀደም ሲል በገብስ ምርት ላይ ብቻ አተኩረው ይሰሩ የነበረውን የግብርና ሥራ እንዲቀይሩ ምክንያት እንደሆኗቸው ይገልጻሉ። ከአርሶ አደር ወልዴ በወሰዱት ልምድ ወደ ጥምር ግብርና ገብተዋል። በዚህም ድርቅ የመቋቋም አቅም ያለውን እንሰት በማሳቸው በስፋት ማልማት ጀምረዋል። የነበሯቸውን ሀገረሰብ የዳልጋ ከብቶች በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በመቀየር የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው እየሰሩ ነው። ጥምር ግብርና የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ከአርሶ አደር ወልዴ ተምሪያለሁ ይላሉ። ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባለፈ የመሬት ለምነትን ለማስጠበቅም ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ የጀመርነውን ሥራ እናጠናክራለን ሲሉም ነው የገለጹት።   የሙህር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ መኑር ጀማል በበኩላቸው "አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ በውስን መሬት ገብስ፣ እንሰት፣ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በጥምር በማልማት የራሳቸውን ህይወት ከመቀየር ባለፈ ለሌሎች አርሶ አደሮች አርአያ እየሆኑን ነው ብለዋል። አርሶ አደሩ በሽታ መቋቋም የሚችሉና ለመድሃኒትነት የሚፈለጉ የእንሰት ዝርያዎችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ በመጥፋት ላይ የነበሩ የእንሰት ዝርያዎችን የመታደግና የአፈር ለምነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የጥምር ግብርና አሰራር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ በመሆኑ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት። የአርሶ አደር ወልዴ ልምድን በማስፋት የሌሎች አርሶ አደሮችም ጓዳ ሞልቶ እንዲትረፈረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጥምር ግብርና አርሶ አደሩ ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ጭምር እንዲተርፍ የማድርጉ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል።   ልማቱ እርስ በእርስ የሚደጋገፉና በአንድ መሬት ላይ የተለያዩ ምርቶችን በማግኘት የተሻለ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚሰራው ሥራ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ በጥቂት መሬት ብዙ ማምረት መቻል ነው። በመሆኑም በተለይ የመሬት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በሥራ ውጤታማ ለመሆን ሁሉም ነገር ምቹና አልጋ በአልጋ መሆን የግድ እንዳልሆነ አርሶ አደሩ ጥሩ ማሳያ ናቸው። ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ዕድል እንዴት ወደሀብትነት መቀየር እችላለሁ ብለው ከሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ የእሳቸው የስኬት ጉዞ በቂ ማሳያ ነው። ሰርቶ ለመለወጥም ሆነ ሀብት ለማፍራት ችግሮችን በጽናት ማለፍ እና የሥራ ትጋት ወሳኝ ነውና ተሞክሯቸውን ማስፋት ያስፈልጋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም