ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በኦሮሚያ ክልል የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ተጀመረ
Dec 12, 2025 13
ማያ ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ዛሬ ተጀመረ። አራተኛው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻው የፌዴራልና የክልሉ የሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በማያ ከተማ አስተዳደር ተጀመሯል። በማያ ከተማ አስተዳደር ሐረማያ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ዳንዲ ቦሩ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በመገኘት ክትባቱን ያስጀመሩት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዶክተር ተስፋዬ ክበበው ፣ የማያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢፍራህ ወዚር (ዶ/ር) እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ናቸው።   ምክትል ሃላፊው ዶክተር ተስፋዬ ክበበው በወቅቱ እንዳሉት፤ በክትባት ዘመቻው በክልሉ ዕድሜያቸው እስከ አምስት ዓመት የሆናቸው 10 ነጥብ 4 ሚሊየን የሚደርሱ ሕፃናት ተጠቃሚ ይሆናሉ። ዘመቻው ተደራሽ የሚሆነው በክልሉ ሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች መሆኑንም አክለዋል። የክትባት ዘመቻውን ለማስፈጸም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን አመልክተው፤ ለዚህም በቂ ባለሙያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች እንዲሁም አስፈላጊው ግብዓት መሟላቱን ገልፀዋል።   ቤት ለቤት ከሚካሄደው የክትባት ዘመቻ ጎን ለጎን ክትባት ያልጀመሩና ጀምረው ያልጨረሱ ህፃናትን የመለየትና ወደ ጤና ተቋማት እንዲሄዱ የማድረግ ስራ እንደሚከናወን የተናገሩት ምክትል ኃላፊው፤ ሌሎች ከጤና ጋር የተያያዙ ክስተቶችን የመለየት ተግባርም ይከናወናል ብለዋል።   የማያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢፍራህ ወዚር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዘመቻውን የተሳካ ለማድረግ በየደረጃው ካሉ የአመራር አካላት ጋር በመቀናጀት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ግብአቶችንና የሰው ኃይል ከማሟላት ባለፈም ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥና የመቀስቀስ ሥራ መከናወኑን አክለዋል።
ኢትዮጵያ በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መጥቷል
Dec 12, 2025 21
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምትሳትፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መምጣቱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ አፍሪካ - ጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ በአፍሪካና ኢትዮጵያ ተስፋዎች እና በመደመር እሳቤ ዙሪያ ንግግር ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ተፅዕኖ ፈጣሪነቷ በግልፅ ታይቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ወቅት ያደረጉት ንግግርና ውይይቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ ከፍታና ተደማጭነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መምጣቱን ገልጸው፤ ከቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች ጋር ፍሬያማ የጎንዮሽ ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤና የሁለትዮሽ ውይይቶች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ የአፍሪካ የጋራ ጉዳዮችን የተመለከቱ መልዕክቶች መተላለፋቸውን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ያስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አጀንዳ ሰጪ መሆኗን በግልጽ አሳይቷል ብለዋል፡፡   የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከሀገር በቀል እሳቤ የተቀዳ ለአፍሪካ ሞዴል እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ማድረጓን ገልጸው፤ ከለውጡ በኋላ በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች የተመዘገቡ ውጤታማ ተግባራትን አንጸባርቃለች ብለዋል፡፡ የመደመር እሳቤ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን የሚበጅ መሆኑን በመጥቀስ፤ አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት እሳቤ ለመውጣት መነሻ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
ሙስናን የመከላከል ትግልን መላው ማህበረሰብና ተቋማት በባለቤትነት ሊይዙት ይገባል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Dec 12, 2025 19
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፦ሙስናን የመከላከል ትግልን መላው ማህበረሰብና ሁሉም ተቋማት በባለቤትነት ሊይዙት እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳሰቡ። 22ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን “ትውልድን በስነ-ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በአዲስ አበባ ደረጃ ተከብሯል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ቀኑን ስናከብር ሙስናን ለመዋጋት ያለንን ቁርጠኝነት እና የገባነውን ቃል በማደስ ሊሆን ይገባል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሙስናን የብልፅግናችን ፀር፣ የኢፍትሀዊነት ምንጭ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ አድርገን ያፋፋምነው ትግል ከዚህ ቀደም የነበረን አስከፊ መንግስታዊ የተደራጀ ሌብነትን ማስቀረት አስችሏል ሲሉ ገልጸዋል።   በዚህም እንደ አገር ብሎም እንደ ከተማ የህዝብና የመንግስትን ሀብት በተገቢው የልማት ስራዎች ላይ መዋሉ አስደናቂ የልማት ውጤቶች ማሳየት መቻሉን አመልክተዋል። መንግስታዊ / ስርአታዊ የተደራጀ ሌብነትን ማስቀረት ብንችልም፣ በግለሰብ ደረጃ የሚታይ በመንግስት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች የሚፈፀመው ሌብነት እና ጉበኝነት ከፍተኛ ትኩረት ይሻል ነው ያሉት። ለሙስና አጋላጭ አሰራሮችን ለመዝጋት እና ከምንጩ ለማድረቅ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በማጠናከር፣ መንግስታዊ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆንና ተጠያቂነትን በማስፈን ሙስናን በተሟላ መልክ ለመከላከል የሁሉንም ተቋማት ትግል እና የሁሉንም ሕብረተሰብ ክፍል ከፍተኛ ርብርብ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።   ቤተሰብ፣ማህበረሰቡ፣የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ የመንግስት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበራት እና ሌሎችም ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ በፀረ ሙስና ትግል ውስጥ በአመለካከትም በተግባርም ሙስናን የሚጠየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር የማይተካ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል። በመሆኑም የፀረ ሙስና ትግሉን ይበልጡን ውጤታማ እንዲሆን የተጀመሩ የሪፎርም ተግባራትን ማጠናከር አስፈላጊ እንደሆነም ነው ከንቲባዋ የገለጹት።
የጤና አገልግሎቱን ከሰው ሰራሽ አስተውሎትና ቴሌ ጤና ጋር በማቀናጀት ተደራሽ እየተደረገ ነው
Dec 12, 2025 16
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦የጤና አገልግሎት ከሰው ሰራሽ አስተውሎትና ቴሌ ጤና ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሒ ገለፁ። ጤና ሚኒስቴር "የሰው ሰራሽ አስተውሎትና የቴሌ ጤና ቴክኖሎጂ ለጤናው ዘርፍ የሚኖራቸው የወደፊት ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ የባለድርሻ አካላት ውይይት እያካሄደ ይገኛል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሒ እንደገለፁት፥ መንግስት የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ይህንን ይበልጥ ለማጠናከር በጤናው ዘርፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን ጥቅም ላይ በማዋል ጥራቱ የተረጋገጠ አገልግሎት እየተሰጠ ስለመሆኑም ጠቁመዋል። ለህክምና አገልግሎት የሚሰበሰቡ መረጃዎች ላይ በመመስረት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማጠናከር የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን መጠቀም ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። በተለይም በወረርሽኝ እና በተፈጥሮ አደጋዎች ቅድመ ትንበያና የተቀናጀ ምላሽ አሰጣጥ ላይ አይነተኛ ሚና እንዳለውም ጠቁመዋል። የጤና ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር አዳዲስና ፈጠራ የታከለባቸው ቴክኖሎጂዎች በተገቢው መልኩ ተግባራዊ እየተደረጉ ስለመሆኑም አንስተዋል። በ2016 ዓ.ም የተሻሻለው አዲሱ የጤና ፖሊሲ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ በተገቢው መልኩ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚደግፍ መሆኑ ለአተገባበሩ አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ነው የጠቀሱት። በተለይም ለጤና ምርመራ፣በታካሚዎች መረጃና የህክምና ታሪክ ላይ የተመሠረተ አገልግሎት ለመስጠትና በርቀት ለሚሰሩ የቴሌ ጤና አገልግሎት መጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ይህም በጤናው ዘርፍ በ2030 ለማሳካት የተቀመጠውን ግብ ከዳር ለማድረስ አይነተኛ ሚና እንዳለው ሚኒስትር ዴኤታዋ አብራርተዋል። ዓለም አቀፍ ሁኔታን ያገናዘበ የጤና ስርዓት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የሚታይ
ኢትዮጵያ በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መጥቷል
Dec 12, 2025 21
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምትሳትፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መምጣቱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ አፍሪካ - ጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ በአፍሪካና ኢትዮጵያ ተስፋዎች እና በመደመር እሳቤ ዙሪያ ንግግር ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ተፅዕኖ ፈጣሪነቷ በግልፅ ታይቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ወቅት ያደረጉት ንግግርና ውይይቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ ከፍታና ተደማጭነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መምጣቱን ገልጸው፤ ከቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች ጋር ፍሬያማ የጎንዮሽ ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤና የሁለትዮሽ ውይይቶች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ የአፍሪካ የጋራ ጉዳዮችን የተመለከቱ መልዕክቶች መተላለፋቸውን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ያስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አጀንዳ ሰጪ መሆኗን በግልጽ አሳይቷል ብለዋል፡፡   የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከሀገር በቀል እሳቤ የተቀዳ ለአፍሪካ ሞዴል እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ማድረጓን ገልጸው፤ ከለውጡ በኋላ በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች የተመዘገቡ ውጤታማ ተግባራትን አንጸባርቃለች ብለዋል፡፡ የመደመር እሳቤ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን የሚበጅ መሆኑን በመጥቀስ፤ አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት እሳቤ ለመውጣት መነሻ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
ሙስናን የመከላከል ትግልን መላው ማህበረሰብና ተቋማት በባለቤትነት ሊይዙት ይገባል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Dec 12, 2025 19
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፦ሙስናን የመከላከል ትግልን መላው ማህበረሰብና ሁሉም ተቋማት በባለቤትነት ሊይዙት እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳሰቡ። 22ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን “ትውልድን በስነ-ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በአዲስ አበባ ደረጃ ተከብሯል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ቀኑን ስናከብር ሙስናን ለመዋጋት ያለንን ቁርጠኝነት እና የገባነውን ቃል በማደስ ሊሆን ይገባል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሙስናን የብልፅግናችን ፀር፣ የኢፍትሀዊነት ምንጭ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ አድርገን ያፋፋምነው ትግል ከዚህ ቀደም የነበረን አስከፊ መንግስታዊ የተደራጀ ሌብነትን ማስቀረት አስችሏል ሲሉ ገልጸዋል።   በዚህም እንደ አገር ብሎም እንደ ከተማ የህዝብና የመንግስትን ሀብት በተገቢው የልማት ስራዎች ላይ መዋሉ አስደናቂ የልማት ውጤቶች ማሳየት መቻሉን አመልክተዋል። መንግስታዊ / ስርአታዊ የተደራጀ ሌብነትን ማስቀረት ብንችልም፣ በግለሰብ ደረጃ የሚታይ በመንግስት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች የሚፈፀመው ሌብነት እና ጉበኝነት ከፍተኛ ትኩረት ይሻል ነው ያሉት። ለሙስና አጋላጭ አሰራሮችን ለመዝጋት እና ከምንጩ ለማድረቅ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በማጠናከር፣ መንግስታዊ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆንና ተጠያቂነትን በማስፈን ሙስናን በተሟላ መልክ ለመከላከል የሁሉንም ተቋማት ትግል እና የሁሉንም ሕብረተሰብ ክፍል ከፍተኛ ርብርብ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።   ቤተሰብ፣ማህበረሰቡ፣የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ የመንግስት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበራት እና ሌሎችም ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ በፀረ ሙስና ትግል ውስጥ በአመለካከትም በተግባርም ሙስናን የሚጠየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር የማይተካ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል። በመሆኑም የፀረ ሙስና ትግሉን ይበልጡን ውጤታማ እንዲሆን የተጀመሩ የሪፎርም ተግባራትን ማጠናከር አስፈላጊ እንደሆነም ነው ከንቲባዋ የገለጹት።
የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነትን ለመቀነስ...
Dec 12, 2025 92
በአብዛኛው ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑት የፋይናንስ ተቋማት እና ባንኮች መሆናቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር አስገነዘበ። በአስተዳደሩ የሳይበር መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መሀመድ ፈረጃ፤ የፋይናንስ ተቋማት፣ሚኒስቴሮች፣ የሕክምና ተቋማት፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ተቋማት፣ የጸጥታና ደኅንነት ተቋማት እንዲሁም ሚዲያዎች በተደጋጋሚ የጥቃት ዒላማ እንደሚደረጉም ተናግረዋል። ስለዚህም የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ቁልፍ የመሠረተ-ልማት ተቋማትን የሚመሩ አካላት ዘርፉን ወይም ተቋም ተኮር የሳይበር ደኅንነት ፖሊሲዎችን እና ፍሬም ወርኮችን መንደፍ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ከዚህም በተጨማሪ ስታንዳርዶችን እንዲቀርጹ እና አሠራሮች እንዲኖሯቸው ይጠበቃል ነው ያሉት። እነዚህን የአሠራር ሥርዓቶች ወደ መሬት ለማውረድ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል እና መሠረተ-ልማቱን ለመጠበቅ የሚያስችል ቴክኖሎጂ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል። በሰው፣ በአሠራር ሥርዓት እና በቴክኖሎጂ ተቋማት ራሳቸውን ዝግጁ ማድረግ እንዳለባቸውም መክረዋል። የሳይበር ደኅንነትን በተቋማት ለማረጋገጥ ዝቅተኛ የሚባሉትን የደኅንነት መስፈርቶች (Baseline) ማሟላት እና ተግባራዊነታቸውን መከታተል እንደሚጠበቅም አመላክተዋል። ይህንም ለማስቻልም መደበኛ የደኅንነት ዳሰሳና ኦዲት ማከናወን እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ጠንካራ የመከላከል ዐቅም ለመገንባት የ‘ዜሮ ትረስት’ መርኅን ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ይህ ማለትም ቀደም ሲል ስጋት ከውጭ እንጅ ከውስጥ የለም የሚል እንደነበር አውስተው፤ የ‘ዜሮ ትረስት’ መርኅ ግን “ማንንም አለማመን እና ሁሉንም ማረጋገጥ” በሚል የተመሰረት ሲሆን ይህም ስጋት ከውስጥም ከውጭም እንዳለ አምኖ መሥራት ነው ብለዋል። ከላይ ከተገለጹት ጥንቃቄዎች አልፎ የሳይበር ጥቃት ሊያጋጥም እንደሚችል እና የጥቃት ጉዳቱን ለመቀነስ እንዲሁም በጋራ ለመመከት እንዲቻል ከተቋማችን ጋር በቅርበት መሥራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። በአብዛኛው ጊዜ ለሳይበር ጥቃት ተጋላጭ የሆኑት የፋይናንስ ተቋማት እና ባንኮች መሆናቸውን ዓመታዊ የሳይበር ጥቃት ሪፖርታችን ያመለክታል ብለዋል።
ለወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በአማካይ 13 ነጥብ 9 በመቶ የስኳር ይዘት ያለው የሸንኮራ አገዳ እየቀረበ ነው
Dec 12, 2025 110
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 2/2018 (ኢዜአ)፡-ለወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በአማካይ 13 ነጥብ 9 በመቶ የስኳር ይዘት ያለው የሸንኮራ አገዳ እየቀረበ መሆኑ ተገልጿል። የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እዩኤል ለላንጎ፤ ሸንኮራ አገዳ ወደ ፋብሪካው የሚያጓጉዙ ማሽነሪዎች እና የፋብሪካው የጥገና ሥራ መጠናቀቁን ተከትሎ የማምረት ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል። በዚህም መሠረት ፋብሪካው የስኳር ምርት እያወጣ መሆኑን ሃላፊው ለኢዜአ ተናግረዋል።   ፋብሪካው በያዝነው በጀት ዓመት ሸንኮራ አገዳ ፈጭቶ በ21 ሠዓት ከ20 ደቂቃ ውስጥ ስኳር ማምረት መቻሉን ጠቁመዋል። ይህም በሀገራችን የስኳር ኢንዱስትሪ ታሪክ በአጭር ጊዜ የስኳር ምርት የተገኘበት ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል ብለዋል። ፋብሪካው በጥራት በመጠገኑ፣ ሸንኮራ አገዳው ጥራት ያለው እና አቅርቦቱም ባልተቆራረጠ ሁኔታ በመቅረቡ የተገኘ ውጤት ስለመሆኑም ተናግረዋል። የስኳር ምርት ለማውጣት ቀደም ሲል 78 ሠዓት፣ በ2016 ዓ.ም 30 ሠዓት እንዲሁም በ2017 ዓ.ም 28 ሠዓት ይፈጅ እንደነበርም አውስተዋል።   የሸንኮራ አገዳዎችን ዝርያ የማሻሻል፣ሸንኮራ አገዳ የመፍጨት፣ ስኳር የማምረት ዐቅምና የጨመቃ ሂደት ላይ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ሥራዎች በጥገና ወቅት መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። ለዘንድሮው ስኳር የማምረት ሥራ በአማካይ 13 ነጥብ 9 በመቶ የስኳር ይዘት ያለው የሸንኮራ አገዳ ለፋብሪካው እየቀረበ መሆኑንም አመላክተዋል።
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ያለ ልዩነት መረባረብ ይገባል 
Dec 12, 2025 115
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ በዘመናት መካከል አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ዕድል በመሆኑ ለስኬቱ ያለ ልዩነት ልንረባረብ ይገባል ሲል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ (National Plenary) ለመጀመር የሚያስችለውን ዝግጅት እያጠናቀቀ እንደሚገኝ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገው ውይይት ተገልጿል።   በውይይቱ የትግራይ ክልልን ጨምሮ አንዳንድ ቀሪ ተግባራትን ፈጥኖ በማጠናቀቅ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በአጭር ጊዜ ማስጀመር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። በትግራይ ክልል ወደ ምክክር ለመግባት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በተደራጀ መንገድ መከናወናቸው፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ የተለያዩ የቅድመ አጀንዳ ማሰባሰቢያ መድረኮች መካሄዳቸውና ከመድረኮቹም ጠቃሚ ግብዓቶች መገኘታቸው ተነስቷል። በክልሉ አጀንዳ በማሰባሰብ እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎችን በማስመረጥ ምክክሩን ምሉዕ ለማድረግ የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገባ ሥነ-ዘዴን በመጠቀም ቀሪ ሥራዎችን ማጠናቀቅ እንዲቻል በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከመግባባት ላይ መደረሱም ተገልጿል። ለዚህም መላው የትግራይ ህዝብ፣ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል ለሚያከናውነው አጀንዳ የማሰባሰብ እና የጉባኤ ተሳታፊዎችን የማስመረጥ ሥራ የበኩላቸውን ቀና ትብብር እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።   የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ታሪካዊ፣ ከአንድ ትውልድ የተሻገረ፣ ከአንድ ፓርቲና ከአንድ ሥርዓት በላይ ከፍ ያለ፣ በዘመናት መካከል አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ዕድል እና ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን የገለጸው ምክር ቤቱ፤ መላው ኢትዮጵያውያን ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ያለልዩነት እንዲረባረቡ መልዕክት አስተላልፏል። የሰላም በሩ ዛሬም ክፍት እንደሆነ በመግለጽም፣ ማንኛውም የፖለቲካ ጥያቄ አለኝ የሚል አካል እና በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ውስጥ የሚገኙ የታጠቁ ኃይሎች ጭምር በሰላማዊ መልኩ ጥያቄያቸውን በአጀንዳነት ለምክክር ኮሚሽኑ እንዲያቀርቡ በድጋሚ ጥሪ አቅርቧል። የቆየውን ኋላ ቀር የፖለቲካ ባህላችንን ከመሠረቱ ለመቀየር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን አዎንታዊ ሚና እንዲጫወት ጥሪ በማስተላለፍ ምክር ቤቱ ውይይቱን አጠናቅቋል። በውይይቱ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ፣ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና እና ምክትልን ጨምሮ ሁሉም ኮሚሽነሮች፣ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መጥቷል
Dec 12, 2025 21
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምትሳትፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መምጣቱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ አፍሪካ - ጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ በአፍሪካና ኢትዮጵያ ተስፋዎች እና በመደመር እሳቤ ዙሪያ ንግግር ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ተፅዕኖ ፈጣሪነቷ በግልፅ ታይቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ወቅት ያደረጉት ንግግርና ውይይቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ ከፍታና ተደማጭነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መምጣቱን ገልጸው፤ ከቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች ጋር ፍሬያማ የጎንዮሽ ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤና የሁለትዮሽ ውይይቶች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ የአፍሪካ የጋራ ጉዳዮችን የተመለከቱ መልዕክቶች መተላለፋቸውን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ያስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አጀንዳ ሰጪ መሆኗን በግልጽ አሳይቷል ብለዋል፡፡   የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከሀገር በቀል እሳቤ የተቀዳ ለአፍሪካ ሞዴል እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ማድረጓን ገልጸው፤ ከለውጡ በኋላ በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች የተመዘገቡ ውጤታማ ተግባራትን አንጸባርቃለች ብለዋል፡፡ የመደመር እሳቤ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን የሚበጅ መሆኑን በመጥቀስ፤ አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት እሳቤ ለመውጣት መነሻ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
ምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው
Dec 12, 2025 17
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከክልል የፖለቲካ የጋራ ምክር ቤቶች ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። በመድረኩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የክልል የጋራ ምክር ቤቶች የ2017 ዓመታዊ ሪፖርት እና የ2018 ዕቅድ ማዕቀፍ ቀርቦ ውይይት እንደሚካሄድበት ተገልጿል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቱ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል። ምክር ቤቱ ሀገራዊ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማ እንዲሆን አጀንዳ አሰባስቦ ከማቅረብ ጀምሮ ከኮሚሽኑ ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ገለልተኛና ግልጽ እንዲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑንም አመላክተዋል።
ዘላቂ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች የበደሉትን ሕዝብ በልማት እንዲክሱ የማመቻቸት ተግባር እየተከናወነ ነው
Dec 12, 2025 19
ጎንደር፤ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የዘላቂ ሰላም ስምምነቱን ተከትሎ የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችን የተሃድሶ ስልጠና ወስደው የበደሉትን ሕዝብ በልማት ለመካስና ሕይወታቸውን እንዲቀይሩ የማመቻቸት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ የሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ። ቀደም ሲልም የሰላም አማራጭን ተከትለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው እራሳቸውን እንዲችሉ ሰፊ ጥረትና ድጋፍ መደረጉም ተመልክቷል። የክልሉ መንግስት እና የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት መካከል ዘላቂ የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወቃል፡፡ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ አንተነህ ታደሰ ለኢዜአ እንዳስታወቁት፤ ስምምነቱን ተከትሎ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች ሰላምን አማራጭ በማድረግ ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት በማስረከብ ተመልሰዋል። የተመለሱትም በተሳሳተ መንገድ በሕዝቡ ላይ በደል በመፈጸማቸው በመፀፀት የሰላምን አማራጭ በመከተላቸው እንደሆነ ገልጸዋል። በወገራ፣ በኪንፋዝ በገላ፣ በአለፋ፣ በጎንደር ዙሪያ፣ በጭልጋና በታች አርማጭሆ ወረዳዎች የተመለሱት የቀድሞ ታጣቂዎቹ የተሃድሶ ስልጠና ወስደው የበደሉትን ሕዝብ በልማት በመካስ ሕይወታቸውን እንዲቀይሩ የማመቻቸት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህም ውስጥ በወገራ ወረዳ ለቀድሞ ታጣቂዎቹ የተሃድሶ ስልጠና መስጠት መጀመሩን ጠቅሰው፤ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። መንግስት የሰላም አማራጭን በመከተል የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም በኩል ባለፈው ዓመት ወደ ቀደመ ስራቸው የተመለሱ እንዳሉም አውስተዋል። የቀድሞ ታጣቂዎቹ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው እራሳቸውን እንዲችሉና ህይወታቸውንም እንዲመሩ መንግስት ሰፊ ጥረትና ድጋፍ ማድረጉንም ተናግረዋል። ሕብረተሰቡ ሰላሙን ለማፅናት እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንዲቀጥል አመልክተው፤ የሰላምን አማራጭ በማይቀበሉ የሽፍታ ሰብስቦች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናከሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ያለ ልዩነት መረባረብ ይገባል 
Dec 12, 2025 115
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ በዘመናት መካከል አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ዕድል በመሆኑ ለስኬቱ ያለ ልዩነት ልንረባረብ ይገባል ሲል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ (National Plenary) ለመጀመር የሚያስችለውን ዝግጅት እያጠናቀቀ እንደሚገኝ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገው ውይይት ተገልጿል።   በውይይቱ የትግራይ ክልልን ጨምሮ አንዳንድ ቀሪ ተግባራትን ፈጥኖ በማጠናቀቅ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በአጭር ጊዜ ማስጀመር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። በትግራይ ክልል ወደ ምክክር ለመግባት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በተደራጀ መንገድ መከናወናቸው፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ የተለያዩ የቅድመ አጀንዳ ማሰባሰቢያ መድረኮች መካሄዳቸውና ከመድረኮቹም ጠቃሚ ግብዓቶች መገኘታቸው ተነስቷል። በክልሉ አጀንዳ በማሰባሰብ እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎችን በማስመረጥ ምክክሩን ምሉዕ ለማድረግ የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገባ ሥነ-ዘዴን በመጠቀም ቀሪ ሥራዎችን ማጠናቀቅ እንዲቻል በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከመግባባት ላይ መደረሱም ተገልጿል። ለዚህም መላው የትግራይ ህዝብ፣ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል ለሚያከናውነው አጀንዳ የማሰባሰብ እና የጉባኤ ተሳታፊዎችን የማስመረጥ ሥራ የበኩላቸውን ቀና ትብብር እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።   የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ታሪካዊ፣ ከአንድ ትውልድ የተሻገረ፣ ከአንድ ፓርቲና ከአንድ ሥርዓት በላይ ከፍ ያለ፣ በዘመናት መካከል አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ዕድል እና ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን የገለጸው ምክር ቤቱ፤ መላው ኢትዮጵያውያን ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ያለልዩነት እንዲረባረቡ መልዕክት አስተላልፏል። የሰላም በሩ ዛሬም ክፍት እንደሆነ በመግለጽም፣ ማንኛውም የፖለቲካ ጥያቄ አለኝ የሚል አካል እና በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ውስጥ የሚገኙ የታጠቁ ኃይሎች ጭምር በሰላማዊ መልኩ ጥያቄያቸውን በአጀንዳነት ለምክክር ኮሚሽኑ እንዲያቀርቡ በድጋሚ ጥሪ አቅርቧል። የቆየውን ኋላ ቀር የፖለቲካ ባህላችንን ከመሠረቱ ለመቀየር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን አዎንታዊ ሚና እንዲጫወት ጥሪ በማስተላለፍ ምክር ቤቱ ውይይቱን አጠናቅቋል። በውይይቱ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ፣ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና እና ምክትልን ጨምሮ ሁሉም ኮሚሽነሮች፣ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለቀጣናዊ ትስስር እና ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል
Dec 12, 2025 86
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለቀጣናዊ ትስስር እና ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) አሳሰቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአምባሳደሮች ኮሚቴ ስብሰባ ትናንት በጅቡቲ ተካሄዷል።   በስብሰባው ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) እና የአምባሳደሮች ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል። የአምባሳደሮች ኮሚቴ የኢጋድ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2030 የሚቆይ ስትራቴጂ አፅድቋል። በተጨማሪም ኮሚቴው የ2026 የኢጋድ በጀት ላይ በመምከር ወደ ስራ እንዲገባ ወስኗል። የቀጣናዊ ተቋሙ ቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ሰላማዊ፣ የተሳሰረ እና ለፈተናዎች የማይበገር ቀጠና ለመገንባት የሀገራት የጋራ ትብብር እና ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።   በተያያዘም የኢጋድ የአምባሳደሮች ኮሚቴ ከስብሰባው ጎን ለጎን የኢጋድ አዲሱን ዋና መስሪያ ቤት የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል። የመሰረተ ልማት ግንባታው ተቋማዊ አቅም እና የጋራ ትብብር ለማጠናከር እንደሚያስችል ዋና ፀሐፊው መናገራቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የኢጋድ የአምባሳደሮች ኮሚቴ የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶችን ያቀፈ ነው። ኢጋድን ማማከር፣ የፖሊሲ ተፈጻሚነት ክትትል እና ድጋፍ፣ የአባል ሀገራት አሰራርን የተቀናጀ ማድረግ፣ ምክረ ሀሳቦች እና የውሳኔ ሀሳቦችን ማቅረብ ወይም ማፅደቅ የኮሚቴው ዋና ተግባራት ናቸው።
በኢትዮጵያ የዳበረ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ እንዲጎለብት እየተሠራ ነው
Dec 11, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የዳበረ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ምክር ቤቱ ያዘጋጀው'' የፖለቲካ ተሳትፎ መመሪያ መፅሐፍ ''ተመርቋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ምክር ቤቱ በሀገሪቱ ጠንካራ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው።   የፖለቲካ ፓርቲዎች ብቁና ዝግጁ ሆነው በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ጠንካራ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሚያስችል የፖለቲካ ተሳትፎ መመሪያ መፅሐፍ መዘጋጀቱን ገልፀዋል። ጠንካራ እና አማራጭ እሳቤን ማቅረብ፣ የተሳካ የህዝብ ግንኙነትን በሚገባ መተግበር፣ የአካታችነትና አሳታፊነትን ባህል መገንባትን ጨምሮ ለስኬታማ የፖለቲካ ምህዳር ወሳኝ የሆኑ ሰፋፊ ተግባራትን እንደሚያጠቃልልም ነው የገለፁት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ በበኩላቸው፤ የመመሪያ መፅሐፉ ፓርቲዎች በምርጫ ሂደት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲሁም የውስጠ ፓርቲ አስተዳደርን መያዙን ጠቅሰዋል።   በመሆኑም የፖለቲካ ፓርቲዎች በመደበኛ ጊዜያቸው ከሚያከናውኗቸው ተግባራት በተጨማሪ ለሀገራዊ ምርጫ ተሳትፏቸው አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል። መጽሐፉ በፖለቲካ ፖርቲዎች መካከል የሚፈጠሩ ችግሮች ቶሎ እንዲፈቱ የምርጫ ቅስቀሳ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ቀድሞ በመለየት መፍትሔ ለማስቀመጥና የፖለቲካ አለመግባባቶች ወደ ግጭት እንዳያመሩ ለማድረግ እንደሚያግዝ ጠቅሰዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች መመሪያ መፅሐፉን በመጠቀም እና በማዳበር ለሀገሪቱ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። በተጨማሪም የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ምክር ቤቱና እርስ በእርስ ስለሚኖራቸው ግንኙነት በተመለከተ የፖለቲካ ተሳትፎ መመሪያ መፅሐፉ ሐሳቦችን መያዙን ተናግረዋል።
በመደመር መንግስት እሳቤ የሀገርን የብልፅግና ጉዞ ለማሳካት እንሰራለን - አመራሮች
Dec 11, 2025 93
ሰቆጣ፣ ገንዳ ውሃ፣ ደብረ ብርሃን፣ ወልዲያ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በመደመር መንግስት እሳቤ የአካባቢን ፀጋ በማልማት የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ የአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢ አመራሮች ገለፁ። ‘’በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ’’ በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና የወሰዱ አመራሮች የማጠቃለያ ፕሮግራምና የልማት ስራዎች ጉብኝት ተካሄዷል። በዋግህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ሰቆጣ ከተማ ስልጠና ተሳታፊዎች መካከል አቶ አሻግሬ ደሳለኝ እና አቶ ታረቀ አለሙ እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት እሳቤ በህብረ ብሄራዊ መርህ ለሀገር ግንባታ መትጋት ነው።   የግብርናውን ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት የመላቀቅ ርዕይን ለማሳካት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ አክለዋል። ሌላዋ የስልጠናው ተሳታፊ ወይዘሮ ፀገነት ደምሴ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው ባገኙት እውቀት ህብረተሰቡ የተፋጠነ አገልግሎት እንዲያገኝ ሚናቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።   በተመሳሳይ በዞኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር የሀገሪቱን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥኑ ናቸው ያሉት ደግሞ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውኃና አካባቢው ያሉ የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሰልጣኞች ናቸው። የጉብኝቱ ተሳታፊ አቤሴሎም ጌታቸው እንዳሉት፤ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነውን አካባቢ ለአልሚዎች ይበልጥ ክፍት እንዲሆን የአመራርነት ሚናቸውን እንደሚወጡም አክለዋል።   ዮናስ ሞላልኝ እና አቶ አስማማው አለባቸው በበኩላቸው፤ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ሀብትን የማመቻቸት ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። መንግስት ያስቀመጣቸውን እድገት ተኮር ኢንሼቲቮች አሟጦ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ እንዳሉት፤ አመራሩ በጉብኝቱ የተመለከቷቸውን የልማት ተግባራት እንደየአካባቢያቸው ነባራዊ ሁኔታ ማስፋትና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢንዱስትሪ ዘርፉን በማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንን የገለፁት ደግሞ የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ደምሰው መንበሩ ናቸው። ባለፉት አምስት ወራት 32 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 211 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል።   የጉብኝቱ ተሳታፊ አቶ ጥላየ ገብርየ እንዳሉት፤ ስልጠናውና በጉብኝቱ ሀገሪቱን ያለችበትን የእድገት ደረጃ ለመገንዘብ ያስቻለ ነው። ስልጠናው ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ኤልሳቤት ሀይለመስቀል ናቸው።   የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው የተገኘውን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አገርን የመገንባትና የማዘመን ስራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከተማችንን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ሃብቶችን ማልማት ላይ ጠንክሮ ለመስራት የቤት ስራ የሰጠ ነው ብለዋል።
አመራሩ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል
Dec 11, 2025 69
ደሴ/ባሕርዳር፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፡-በተደመረ አቅምና እውቀት አመራሩ ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ተናገሩ። "የመደመር መንግስት እይታ፣የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በደሴና ባሕርዳር ለመካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።   በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ፤ በየደረጃው ያለው አመራር ለልማት ከመትጋት ባለፈ በቀናኢነት ህዝብን ለማገልገል የላቀ ዝግጁነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት ጭምር የተሟላ ስብእና በመላበስ ለችግሮች መፍትሄ መሻት፣ለሰላምና ልማት በጋራ መትጋት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን ግንዛቤ በመሰነቅ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል መዘጋጀት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የክልሉ መንግስት ከምንም በላይ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን፣ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሃብትና ጸጋዎችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የማድረግ የተቀናጀ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል።   ከስልጠናው ታሳትፊዎች መካከል ወይዘሮ ሶፊና አደም እና አቶ ኡመር አሰፋ፤ ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት ተግባር ላይ በማዋል ውጤት ለማምጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በባሕርዳር ከተማ የማጠቃለያ መድረክ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን፤ ‎በግብርና፣በኢንዱስትሪ፣ በከተሞች መሰረተ ልማትና በቱሪዝም ብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት ዘርፎች ላይ የተሰጡ ስልጠናዎችን በተቀናጀ መልኩ በተግባር መግለጥ ይገባል ብለዋል።   የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰፋ ጥላሁን፤ ‎የልማት እቅዶችን ማሳካት የሚቻለው በትብብር በመስራት በመሆኑ በዚሁ ልክ አመራሩ ዝግጁ ሆኖ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊ አመራሮችም በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መጥቷል
Dec 12, 2025 21
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምትሳትፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መምጣቱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ አፍሪካ - ጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ በአፍሪካና ኢትዮጵያ ተስፋዎች እና በመደመር እሳቤ ዙሪያ ንግግር ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ተፅዕኖ ፈጣሪነቷ በግልፅ ታይቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ወቅት ያደረጉት ንግግርና ውይይቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ ከፍታና ተደማጭነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ተደማጭነቷ እያደገ መምጣቱን ገልጸው፤ ከቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች ጋር ፍሬያማ የጎንዮሽ ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤና የሁለትዮሽ ውይይቶች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ የአፍሪካ የጋራ ጉዳዮችን የተመለከቱ መልዕክቶች መተላለፋቸውን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ያስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አጀንዳ ሰጪ መሆኗን በግልጽ አሳይቷል ብለዋል፡፡   የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከሀገር በቀል እሳቤ የተቀዳ ለአፍሪካ ሞዴል እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ማድረጓን ገልጸው፤ ከለውጡ በኋላ በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች የተመዘገቡ ውጤታማ ተግባራትን አንጸባርቃለች ብለዋል፡፡ የመደመር እሳቤ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን የሚበጅ መሆኑን በመጥቀስ፤ አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት እሳቤ ለመውጣት መነሻ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
ምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው
Dec 12, 2025 17
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከክልል የፖለቲካ የጋራ ምክር ቤቶች ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። በመድረኩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የክልል የጋራ ምክር ቤቶች የ2017 ዓመታዊ ሪፖርት እና የ2018 ዕቅድ ማዕቀፍ ቀርቦ ውይይት እንደሚካሄድበት ተገልጿል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቱ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል። ምክር ቤቱ ሀገራዊ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማ እንዲሆን አጀንዳ አሰባስቦ ከማቅረብ ጀምሮ ከኮሚሽኑ ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ገለልተኛና ግልጽ እንዲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑንም አመላክተዋል።
ዘላቂ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች የበደሉትን ሕዝብ በልማት እንዲክሱ የማመቻቸት ተግባር እየተከናወነ ነው
Dec 12, 2025 19
ጎንደር፤ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የዘላቂ ሰላም ስምምነቱን ተከትሎ የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችን የተሃድሶ ስልጠና ወስደው የበደሉትን ሕዝብ በልማት ለመካስና ሕይወታቸውን እንዲቀይሩ የማመቻቸት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ የሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ። ቀደም ሲልም የሰላም አማራጭን ተከትለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው እራሳቸውን እንዲችሉ ሰፊ ጥረትና ድጋፍ መደረጉም ተመልክቷል። የክልሉ መንግስት እና የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት መካከል ዘላቂ የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወቃል፡፡ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ አንተነህ ታደሰ ለኢዜአ እንዳስታወቁት፤ ስምምነቱን ተከትሎ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች ሰላምን አማራጭ በማድረግ ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት በማስረከብ ተመልሰዋል። የተመለሱትም በተሳሳተ መንገድ በሕዝቡ ላይ በደል በመፈጸማቸው በመፀፀት የሰላምን አማራጭ በመከተላቸው እንደሆነ ገልጸዋል። በወገራ፣ በኪንፋዝ በገላ፣ በአለፋ፣ በጎንደር ዙሪያ፣ በጭልጋና በታች አርማጭሆ ወረዳዎች የተመለሱት የቀድሞ ታጣቂዎቹ የተሃድሶ ስልጠና ወስደው የበደሉትን ሕዝብ በልማት በመካስ ሕይወታቸውን እንዲቀይሩ የማመቻቸት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህም ውስጥ በወገራ ወረዳ ለቀድሞ ታጣቂዎቹ የተሃድሶ ስልጠና መስጠት መጀመሩን ጠቅሰው፤ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። መንግስት የሰላም አማራጭን በመከተል የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም በኩል ባለፈው ዓመት ወደ ቀደመ ስራቸው የተመለሱ እንዳሉም አውስተዋል። የቀድሞ ታጣቂዎቹ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው እራሳቸውን እንዲችሉና ህይወታቸውንም እንዲመሩ መንግስት ሰፊ ጥረትና ድጋፍ ማድረጉንም ተናግረዋል። ሕብረተሰቡ ሰላሙን ለማፅናት እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንዲቀጥል አመልክተው፤ የሰላምን አማራጭ በማይቀበሉ የሽፍታ ሰብስቦች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናከሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ያለ ልዩነት መረባረብ ይገባል 
Dec 12, 2025 115
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ በዘመናት መካከል አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ዕድል በመሆኑ ለስኬቱ ያለ ልዩነት ልንረባረብ ይገባል ሲል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ (National Plenary) ለመጀመር የሚያስችለውን ዝግጅት እያጠናቀቀ እንደሚገኝ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገው ውይይት ተገልጿል።   በውይይቱ የትግራይ ክልልን ጨምሮ አንዳንድ ቀሪ ተግባራትን ፈጥኖ በማጠናቀቅ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በአጭር ጊዜ ማስጀመር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። በትግራይ ክልል ወደ ምክክር ለመግባት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በተደራጀ መንገድ መከናወናቸው፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ የተለያዩ የቅድመ አጀንዳ ማሰባሰቢያ መድረኮች መካሄዳቸውና ከመድረኮቹም ጠቃሚ ግብዓቶች መገኘታቸው ተነስቷል። በክልሉ አጀንዳ በማሰባሰብ እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎችን በማስመረጥ ምክክሩን ምሉዕ ለማድረግ የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገባ ሥነ-ዘዴን በመጠቀም ቀሪ ሥራዎችን ማጠናቀቅ እንዲቻል በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከመግባባት ላይ መደረሱም ተገልጿል። ለዚህም መላው የትግራይ ህዝብ፣ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል ለሚያከናውነው አጀንዳ የማሰባሰብ እና የጉባኤ ተሳታፊዎችን የማስመረጥ ሥራ የበኩላቸውን ቀና ትብብር እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።   የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ታሪካዊ፣ ከአንድ ትውልድ የተሻገረ፣ ከአንድ ፓርቲና ከአንድ ሥርዓት በላይ ከፍ ያለ፣ በዘመናት መካከል አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ዕድል እና ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን የገለጸው ምክር ቤቱ፤ መላው ኢትዮጵያውያን ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ያለልዩነት እንዲረባረቡ መልዕክት አስተላልፏል። የሰላም በሩ ዛሬም ክፍት እንደሆነ በመግለጽም፣ ማንኛውም የፖለቲካ ጥያቄ አለኝ የሚል አካል እና በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ውስጥ የሚገኙ የታጠቁ ኃይሎች ጭምር በሰላማዊ መልኩ ጥያቄያቸውን በአጀንዳነት ለምክክር ኮሚሽኑ እንዲያቀርቡ በድጋሚ ጥሪ አቅርቧል። የቆየውን ኋላ ቀር የፖለቲካ ባህላችንን ከመሠረቱ ለመቀየር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን አዎንታዊ ሚና እንዲጫወት ጥሪ በማስተላለፍ ምክር ቤቱ ውይይቱን አጠናቅቋል። በውይይቱ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ፣ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና እና ምክትልን ጨምሮ ሁሉም ኮሚሽነሮች፣ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለቀጣናዊ ትስስር እና ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል
Dec 12, 2025 86
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለቀጣናዊ ትስስር እና ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) አሳሰቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአምባሳደሮች ኮሚቴ ስብሰባ ትናንት በጅቡቲ ተካሄዷል።   በስብሰባው ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) እና የአምባሳደሮች ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል። የአምባሳደሮች ኮሚቴ የኢጋድ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2030 የሚቆይ ስትራቴጂ አፅድቋል። በተጨማሪም ኮሚቴው የ2026 የኢጋድ በጀት ላይ በመምከር ወደ ስራ እንዲገባ ወስኗል። የቀጣናዊ ተቋሙ ቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ሰላማዊ፣ የተሳሰረ እና ለፈተናዎች የማይበገር ቀጠና ለመገንባት የሀገራት የጋራ ትብብር እና ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።   በተያያዘም የኢጋድ የአምባሳደሮች ኮሚቴ ከስብሰባው ጎን ለጎን የኢጋድ አዲሱን ዋና መስሪያ ቤት የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል። የመሰረተ ልማት ግንባታው ተቋማዊ አቅም እና የጋራ ትብብር ለማጠናከር እንደሚያስችል ዋና ፀሐፊው መናገራቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የኢጋድ የአምባሳደሮች ኮሚቴ የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶችን ያቀፈ ነው። ኢጋድን ማማከር፣ የፖሊሲ ተፈጻሚነት ክትትል እና ድጋፍ፣ የአባል ሀገራት አሰራርን የተቀናጀ ማድረግ፣ ምክረ ሀሳቦች እና የውሳኔ ሀሳቦችን ማቅረብ ወይም ማፅደቅ የኮሚቴው ዋና ተግባራት ናቸው።
በኢትዮጵያ የዳበረ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ እንዲጎለብት እየተሠራ ነው
Dec 11, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የዳበረ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ምክር ቤቱ ያዘጋጀው'' የፖለቲካ ተሳትፎ መመሪያ መፅሐፍ ''ተመርቋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ምክር ቤቱ በሀገሪቱ ጠንካራ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው።   የፖለቲካ ፓርቲዎች ብቁና ዝግጁ ሆነው በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ጠንካራ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሚያስችል የፖለቲካ ተሳትፎ መመሪያ መፅሐፍ መዘጋጀቱን ገልፀዋል። ጠንካራ እና አማራጭ እሳቤን ማቅረብ፣ የተሳካ የህዝብ ግንኙነትን በሚገባ መተግበር፣ የአካታችነትና አሳታፊነትን ባህል መገንባትን ጨምሮ ለስኬታማ የፖለቲካ ምህዳር ወሳኝ የሆኑ ሰፋፊ ተግባራትን እንደሚያጠቃልልም ነው የገለፁት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ በበኩላቸው፤ የመመሪያ መፅሐፉ ፓርቲዎች በምርጫ ሂደት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲሁም የውስጠ ፓርቲ አስተዳደርን መያዙን ጠቅሰዋል።   በመሆኑም የፖለቲካ ፓርቲዎች በመደበኛ ጊዜያቸው ከሚያከናውኗቸው ተግባራት በተጨማሪ ለሀገራዊ ምርጫ ተሳትፏቸው አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል። መጽሐፉ በፖለቲካ ፖርቲዎች መካከል የሚፈጠሩ ችግሮች ቶሎ እንዲፈቱ የምርጫ ቅስቀሳ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ቀድሞ በመለየት መፍትሔ ለማስቀመጥና የፖለቲካ አለመግባባቶች ወደ ግጭት እንዳያመሩ ለማድረግ እንደሚያግዝ ጠቅሰዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች መመሪያ መፅሐፉን በመጠቀም እና በማዳበር ለሀገሪቱ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። በተጨማሪም የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ምክር ቤቱና እርስ በእርስ ስለሚኖራቸው ግንኙነት በተመለከተ የፖለቲካ ተሳትፎ መመሪያ መፅሐፉ ሐሳቦችን መያዙን ተናግረዋል።
በመደመር መንግስት እሳቤ የሀገርን የብልፅግና ጉዞ ለማሳካት እንሰራለን - አመራሮች
Dec 11, 2025 93
ሰቆጣ፣ ገንዳ ውሃ፣ ደብረ ብርሃን፣ ወልዲያ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በመደመር መንግስት እሳቤ የአካባቢን ፀጋ በማልማት የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ የአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢ አመራሮች ገለፁ። ‘’በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ’’ በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና የወሰዱ አመራሮች የማጠቃለያ ፕሮግራምና የልማት ስራዎች ጉብኝት ተካሄዷል። በዋግህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ሰቆጣ ከተማ ስልጠና ተሳታፊዎች መካከል አቶ አሻግሬ ደሳለኝ እና አቶ ታረቀ አለሙ እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት እሳቤ በህብረ ብሄራዊ መርህ ለሀገር ግንባታ መትጋት ነው።   የግብርናውን ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት የመላቀቅ ርዕይን ለማሳካት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ አክለዋል። ሌላዋ የስልጠናው ተሳታፊ ወይዘሮ ፀገነት ደምሴ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው ባገኙት እውቀት ህብረተሰቡ የተፋጠነ አገልግሎት እንዲያገኝ ሚናቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።   በተመሳሳይ በዞኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር የሀገሪቱን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥኑ ናቸው ያሉት ደግሞ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውኃና አካባቢው ያሉ የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሰልጣኞች ናቸው። የጉብኝቱ ተሳታፊ አቤሴሎም ጌታቸው እንዳሉት፤ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነውን አካባቢ ለአልሚዎች ይበልጥ ክፍት እንዲሆን የአመራርነት ሚናቸውን እንደሚወጡም አክለዋል።   ዮናስ ሞላልኝ እና አቶ አስማማው አለባቸው በበኩላቸው፤ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ሀብትን የማመቻቸት ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። መንግስት ያስቀመጣቸውን እድገት ተኮር ኢንሼቲቮች አሟጦ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ እንዳሉት፤ አመራሩ በጉብኝቱ የተመለከቷቸውን የልማት ተግባራት እንደየአካባቢያቸው ነባራዊ ሁኔታ ማስፋትና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢንዱስትሪ ዘርፉን በማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንን የገለፁት ደግሞ የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ደምሰው መንበሩ ናቸው። ባለፉት አምስት ወራት 32 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 211 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል።   የጉብኝቱ ተሳታፊ አቶ ጥላየ ገብርየ እንዳሉት፤ ስልጠናውና በጉብኝቱ ሀገሪቱን ያለችበትን የእድገት ደረጃ ለመገንዘብ ያስቻለ ነው። ስልጠናው ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ኤልሳቤት ሀይለመስቀል ናቸው።   የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው የተገኘውን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አገርን የመገንባትና የማዘመን ስራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከተማችንን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ሃብቶችን ማልማት ላይ ጠንክሮ ለመስራት የቤት ስራ የሰጠ ነው ብለዋል።
አመራሩ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል
Dec 11, 2025 69
ደሴ/ባሕርዳር፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፡-በተደመረ አቅምና እውቀት አመራሩ ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ተናገሩ። "የመደመር መንግስት እይታ፣የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በደሴና ባሕርዳር ለመካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።   በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ፤ በየደረጃው ያለው አመራር ለልማት ከመትጋት ባለፈ በቀናኢነት ህዝብን ለማገልገል የላቀ ዝግጁነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት ጭምር የተሟላ ስብእና በመላበስ ለችግሮች መፍትሄ መሻት፣ለሰላምና ልማት በጋራ መትጋት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን ግንዛቤ በመሰነቅ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል መዘጋጀት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የክልሉ መንግስት ከምንም በላይ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን፣ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሃብትና ጸጋዎችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የማድረግ የተቀናጀ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል።   ከስልጠናው ታሳትፊዎች መካከል ወይዘሮ ሶፊና አደም እና አቶ ኡመር አሰፋ፤ ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት ተግባር ላይ በማዋል ውጤት ለማምጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በባሕርዳር ከተማ የማጠቃለያ መድረክ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን፤ ‎በግብርና፣በኢንዱስትሪ፣ በከተሞች መሰረተ ልማትና በቱሪዝም ብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት ዘርፎች ላይ የተሰጡ ስልጠናዎችን በተቀናጀ መልኩ በተግባር መግለጥ ይገባል ብለዋል።   የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰፋ ጥላሁን፤ ‎የልማት እቅዶችን ማሳካት የሚቻለው በትብብር በመስራት በመሆኑ በዚሁ ልክ አመራሩ ዝግጁ ሆኖ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊ አመራሮችም በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ
በኦሮሚያ ክልል የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ተጀመረ
Dec 12, 2025 13
ማያ ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ዛሬ ተጀመረ። አራተኛው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻው የፌዴራልና የክልሉ የሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በማያ ከተማ አስተዳደር ተጀመሯል። በማያ ከተማ አስተዳደር ሐረማያ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ዳንዲ ቦሩ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በመገኘት ክትባቱን ያስጀመሩት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዶክተር ተስፋዬ ክበበው ፣ የማያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢፍራህ ወዚር (ዶ/ር) እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ናቸው።   ምክትል ሃላፊው ዶክተር ተስፋዬ ክበበው በወቅቱ እንዳሉት፤ በክትባት ዘመቻው በክልሉ ዕድሜያቸው እስከ አምስት ዓመት የሆናቸው 10 ነጥብ 4 ሚሊየን የሚደርሱ ሕፃናት ተጠቃሚ ይሆናሉ። ዘመቻው ተደራሽ የሚሆነው በክልሉ ሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች መሆኑንም አክለዋል። የክትባት ዘመቻውን ለማስፈጸም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን አመልክተው፤ ለዚህም በቂ ባለሙያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች እንዲሁም አስፈላጊው ግብዓት መሟላቱን ገልፀዋል።   ቤት ለቤት ከሚካሄደው የክትባት ዘመቻ ጎን ለጎን ክትባት ያልጀመሩና ጀምረው ያልጨረሱ ህፃናትን የመለየትና ወደ ጤና ተቋማት እንዲሄዱ የማድረግ ስራ እንደሚከናወን የተናገሩት ምክትል ኃላፊው፤ ሌሎች ከጤና ጋር የተያያዙ ክስተቶችን የመለየት ተግባርም ይከናወናል ብለዋል።   የማያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢፍራህ ወዚር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዘመቻውን የተሳካ ለማድረግ በየደረጃው ካሉ የአመራር አካላት ጋር በመቀናጀት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ግብአቶችንና የሰው ኃይል ከማሟላት ባለፈም ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥና የመቀስቀስ ሥራ መከናወኑን አክለዋል።
ሙስናን የመከላከል ትግልን መላው ማህበረሰብና ተቋማት በባለቤትነት ሊይዙት ይገባል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Dec 12, 2025 19
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፦ሙስናን የመከላከል ትግልን መላው ማህበረሰብና ሁሉም ተቋማት በባለቤትነት ሊይዙት እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳሰቡ። 22ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን “ትውልድን በስነ-ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በአዲስ አበባ ደረጃ ተከብሯል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ቀኑን ስናከብር ሙስናን ለመዋጋት ያለንን ቁርጠኝነት እና የገባነውን ቃል በማደስ ሊሆን ይገባል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሙስናን የብልፅግናችን ፀር፣ የኢፍትሀዊነት ምንጭ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ አድርገን ያፋፋምነው ትግል ከዚህ ቀደም የነበረን አስከፊ መንግስታዊ የተደራጀ ሌብነትን ማስቀረት አስችሏል ሲሉ ገልጸዋል።   በዚህም እንደ አገር ብሎም እንደ ከተማ የህዝብና የመንግስትን ሀብት በተገቢው የልማት ስራዎች ላይ መዋሉ አስደናቂ የልማት ውጤቶች ማሳየት መቻሉን አመልክተዋል። መንግስታዊ / ስርአታዊ የተደራጀ ሌብነትን ማስቀረት ብንችልም፣ በግለሰብ ደረጃ የሚታይ በመንግስት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች የሚፈፀመው ሌብነት እና ጉበኝነት ከፍተኛ ትኩረት ይሻል ነው ያሉት። ለሙስና አጋላጭ አሰራሮችን ለመዝጋት እና ከምንጩ ለማድረቅ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በማጠናከር፣ መንግስታዊ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆንና ተጠያቂነትን በማስፈን ሙስናን በተሟላ መልክ ለመከላከል የሁሉንም ተቋማት ትግል እና የሁሉንም ሕብረተሰብ ክፍል ከፍተኛ ርብርብ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።   ቤተሰብ፣ማህበረሰቡ፣የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ የመንግስት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበራት እና ሌሎችም ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ በፀረ ሙስና ትግል ውስጥ በአመለካከትም በተግባርም ሙስናን የሚጠየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር የማይተካ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል። በመሆኑም የፀረ ሙስና ትግሉን ይበልጡን ውጤታማ እንዲሆን የተጀመሩ የሪፎርም ተግባራትን ማጠናከር አስፈላጊ እንደሆነም ነው ከንቲባዋ የገለጹት።
የጤና አገልግሎቱን ከሰው ሰራሽ አስተውሎትና ቴሌ ጤና ጋር በማቀናጀት ተደራሽ እየተደረገ ነው
Dec 12, 2025 16
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦የጤና አገልግሎት ከሰው ሰራሽ አስተውሎትና ቴሌ ጤና ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሒ ገለፁ። ጤና ሚኒስቴር "የሰው ሰራሽ አስተውሎትና የቴሌ ጤና ቴክኖሎጂ ለጤናው ዘርፍ የሚኖራቸው የወደፊት ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ የባለድርሻ አካላት ውይይት እያካሄደ ይገኛል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሒ እንደገለፁት፥ መንግስት የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ይህንን ይበልጥ ለማጠናከር በጤናው ዘርፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን ጥቅም ላይ በማዋል ጥራቱ የተረጋገጠ አገልግሎት እየተሰጠ ስለመሆኑም ጠቁመዋል። ለህክምና አገልግሎት የሚሰበሰቡ መረጃዎች ላይ በመመስረት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማጠናከር የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን መጠቀም ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። በተለይም በወረርሽኝ እና በተፈጥሮ አደጋዎች ቅድመ ትንበያና የተቀናጀ ምላሽ አሰጣጥ ላይ አይነተኛ ሚና እንዳለውም ጠቁመዋል። የጤና ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር አዳዲስና ፈጠራ የታከለባቸው ቴክኖሎጂዎች በተገቢው መልኩ ተግባራዊ እየተደረጉ ስለመሆኑም አንስተዋል። በ2016 ዓ.ም የተሻሻለው አዲሱ የጤና ፖሊሲ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ በተገቢው መልኩ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚደግፍ መሆኑ ለአተገባበሩ አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ነው የጠቀሱት። በተለይም ለጤና ምርመራ፣በታካሚዎች መረጃና የህክምና ታሪክ ላይ የተመሠረተ አገልግሎት ለመስጠትና በርቀት ለሚሰሩ የቴሌ ጤና አገልግሎት መጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ይህም በጤናው ዘርፍ በ2030 ለማሳካት የተቀመጠውን ግብ ከዳር ለማድረስ አይነተኛ ሚና እንዳለው ሚኒስትር ዴኤታዋ አብራርተዋል። ዓለም አቀፍ ሁኔታን ያገናዘበ የጤና ስርዓት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተቀናጀ የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) መከላከያ ክትባት እየተሰጠ ነው
Dec 12, 2025 52
ጂንካ ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተቀናጀ የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) መከላከያ ክትባት እየተሰጠ ነው። የክትባት ዘመቻው ዛሬ መሰጠት የተጀመረው በክልሉ አሪ ዞን ጂንካ ከተማ አስተዳደር ገርተጵ ቀበሌ ነው። የክትባት ዘመቻውን በይፋ ያስጀመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አጉኔ አሾሌ፣ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ምንተስኖት መልካ (ዶ/ር) እና የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ናቸው። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አጉኔ አሾሌ በዚህን ጊዜ እንደገለጹት፤ ፖሊዮ ወይም የልጅነት ልምሻ ለዘላቂ የአካል ጉዳትና ሞት የሚዳርግ አደገኛ በሽታ ነው።   የፖሊዮ በሽታን ለመከላከል ክትባቱን በአግባቡ መውሰድ እንደሚገባ ገልጸው ክትባቱ ዛሬ በዘመቻ መልክ መስጠት መጀመሩን ገልጸዋል። ክትባቱ ከዛሬ ጀምሮ ለአራት ቀናት በሁሉም የክልል አካባቢዎች ቤት ለቤት በመዘዋወር እንደሚሰጥም ተናግረዋል ። በዘመቻው ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ክትባቱ እንደሚሰጥ ገልጸው፣ ሕጻናቱ ከዚህ ቀደም ክትባቱን ቢወስዱም ባይወስዱም በዚህ ዙር መከተብ እንዳለባቸው አስታውቀዋል። ከዘመቻው ጎን ለጎን የሥርዓተ ምግብ ጉድለት ያለባቸው ነፍሰ ጡር እናቶችን እንዲሁም ቆልማማ እግር ያላቸው ሕጻናትን በመለየት ነጻ የሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥም ዳይሬክተሩ አመላክተዋል። የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ በበኩላቸው፤ የፖሊዮ በሽታ ህፃናትን ለአካል ጉዳት እና ሞት የሚዳርግ በመሆኑ ወላጆች ትኩረት ሰጥተው ልጆቻቸውን እንዲያስከትቡ አስገንዝበዋል።   እንደ አስተዳዳሪው ገለጻ ባለፉት ዓመታት ማህበረሰቡን በማሳተፍ የተሰጠው የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት በዞኑ በሽታውን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት አግዟል። በዞኑ የሚካሄደው የክትባት ዘመቻ ውጤታማ እንዲሆን የዞኑ አስተዳደር ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቁመው፣ ዘመቻው ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም የበኩሉን መወጣት አለበት ሲሉ አሳስበዋል።
ኢኮኖሚ
የባሌ ዞን አርሶአደሮች ጥራቱን የጠበቀ ቡና በመሰብሰብ በገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን እየሰሩ ነው
Dec 12, 2025 65
ሮቤ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በባሌ ዞን ጥራቱን የጠበቀ ቡና በመሰብሰብ በገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን እየሰሩ መሆናቸውን በዞኑ የሀረና ቡሉቅ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። በዞኑ በቡና አብቃይ ወረዳዎች ከ44 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የለማውን ቡና ጥራትን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የለቀማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተመላክቷል።   በልማቱ ከተሰማሩ የሀረና ቡሉቅ ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አቶ አህመድ ሁሴን በሰጡት አስተያየት፤ ዘንድሮ ለቡና ጥራት በተሰጠው ትኩረት በቡና አመራረት ሂደት ላይ በተግባር የተደገፈ ሥልጠናና የጥራት ማስጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።   በዚህም የለቀሙትን ቀይ ቡና በድጋፍ ባገኙት የቡና ማድረቅያ ሽቦ ላይ በማድረቅ ከአምና የተሻለ ገቢ ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በቡና ልማት የመሳተፍ የቆየ ልምድ ቢኖራቸውም ከምርጥ ዝርያ አጠቃቀም ምክንያት የልፋታቸውን ያህል ተጠቃሚ እንዳልነበሩ የገለጹት ደግሞ ሌላው የወረዳ አርሶ አደር ኡስማን ማህሙድ ናቸው።   ካለፉት አራት ዓመታት ወዲህ መንግሥት የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን እንዲያገኙ ከማድረግ በተጓዳኝ በአመራረት ሂደትም ቀይ ቡናን ብቻ በመልቀም ጥራት ያለው ቡና ለገበያ እንዲቀርቡ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ በዘርፉ ያላቸው ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። አርሶ አደሮቹ ካለሙት የቡና ምርት ከአንድ ሄክታር ከ9 እስከ 10 ኩንታል የቡና ምርት እንደሚጠብቁም ተናግረዋል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሙአዊያ ፉአድ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የቡናን ምርታማነት በማሳደግ ጥራት ያለው ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አመላክተዋል።   ለዚህም ከልማቱ ባልተናነሰ በቡና አሰባሰብና ክምችት የሚስተዋሉ ግድፈቶችን ለማረም ለአርሶ አደሮችና ባለድርሻ አካላት በቡና ጥራት ላይ ተግባር ተኮር ሥልጠና መሰጠቱን አስታውሰዋል። አርሶ አደሩ የቡና ጥራትን ለማስጠበቅም ቀይ ቡና ብቻ እንዲለቅም፣ በሽቦ አልጋ አሊያም በሲሚንቶ በተሰራ ዐውድማ ላይ እንዲያደርቅ ግንዛቤና የቁሳቁስ ድጋፍ መሰጠቱን አንስተዋል። በዞኑ በአሁኑ ወቅት ከ44 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የለማውን ቡና ጥራትን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የለቀማ ሥራ በማከናወን ከ437 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።   እስከ አሁን በተደረገው ጥረት ከ31 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ቡና መልቀም መቻሉን ጠቁመው ከ312 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ የጥራት ደረጃውን የጠበቀ ቡና መሰብሰብ መቻሉን አስታውሰዋል። ለቡና ምርታማነትና ጥራት በተሰጠው ትኩረት ከአንድ ሄክታር የሚመረተውን ቡና 10 ኩንታል ማድረስ መቻሉን የጠቆሙት ምክትል ኃላፊው÷የጥራት ደረጃውም እየተሻሻለ በመምጣቱ ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበውን ቡና ወደ 15 ሺህ ቶን ከፍ ለማድረግ መታቀዱንም አመልክተዋል። በባሌ ዞን ከ68 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በቡና ተክል የተሸፈነ መሆኑም ተመልክቷል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን የንብ ማነብ ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ሆነዋል
Dec 12, 2025 43
ጊምቢ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦በምዕራብ ወለጋ ዞን ዘመናዊ የአሰራር ዘዴን በመከተል የንብ ማነብ ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡ በማር ልማት የተሰማሩ የዞኑ አርሶ አደሮች ዘመናዊ ቀፎ በመጠቀም ንብ ማነብ ከጀመሩ ወዲህ የማር ምርታቸው እየጨመረ በመምጣቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡ ከአርሶ አደሮቹ መካካል የጊምቢ ወረዳ ነዋሪ አቶ ዳዊት ገመቹ በባህላዊ መንገድ ማር በሚያመርቱበት ጊዜ ተጠቃሚነታቸው እምብዛም እንደነበር ያወሳሉ። አሁን ላይ በተደረገላቸው የባለሙያ ድጋፍ ዘመናዊ አሰራርን በመከተል በግላቸው 21 ዘመናዊ ቀፎ ተጠቅመው ንብ ማነብ ከጀመሩ ወዲህ በዓመት ከ350 ኪሎ ግራም በላይ ማር በማምረት ኑሯቸውን በተሻለ ሁኔታ እየመሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።   የላሎ አሳቢ ወረዳ ነዋሪ አርሶአደር ዋቅቶላ ሰለሞን፤ ባህላዊና ዘመናዊ ቀፎን በመጠቀም ማር እያመረቱ እንደሚገኙ ገልጸው፤ ከአንድ ባህላዊ ቀፎ ከ6 እስከ 8 ኪሎ ግራም ይገኝ የነበረው አሁን ላይ ከአንድ ዘመናዊ ቀፎ ከ25 እስከ 30 ኪሎ ግራም ምርት ማግኘታቸውን አንስተዋል። ዘመናዊ የአሰራር ዘዴን በመጠቀም ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን አንስተው ልማቱን በማስፋት የበለጠ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው የሚሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። አርሶ አደር አያና ካሚሶ በበኩላቸው፤ በባህላዊ ዘዴ ማር በሚያመርቱበት ጊዜ በዓመት በአጠቃላይ ከ20 አስከ 30 ኪሎ ግራም ያልበለጠ ምርት ያገኙ እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡ አሁን ዘመናዊ ቀፎን በመጠቀም ንብ ማነብ ከጀመሩ ወዲህ ከ50 አስከ 70 ኪሎ ግራም የማር ምርት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   በምዕራብ ወለጋ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት የእንስሳት ልማትና ዝርያ ማሻሻያ ቡድን መሪ አቶ ገመቺስ ታደሰ፤ በዞኑ በምርት ዘመኑ ከ12ሺህ ቶን በላይ ማር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።   በዘርፉ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ውጤታማ እንዲሆኑ ዘመናዊ የአሰራር ዘዴን እንዲከተሉ በማድረግና ዘመናዊ የንብ ቀፎን በማከፋፈል እንዲሁም ሙያዊ ድጋፍና ክትትል በማጠናከር መሰራቱን አንስተዋል።   በዚህም በ2018 የምርት ዘመን 116ሺህ 327 ዘመናዊ ቀፎ ለአርሶ አደሩ ለማሰራጨት ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን እስካሁኑ 47ሺህ 387 ቀፎ መከፋፈሉን ተናግረዋል፡፡ በዞኑ በማር ልማቱ 15ሺህ አርሶ አደሮች መሰማራታቸውንም አቶ ገመቺስ ተናግረዋል።
በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ሚሊየነር  የሆነው  ወጣት
Dec 12, 2025 47
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሀገር አቀፍ ደረጃ በአርባ ምንጭ ከተማ ያስጀመሩት የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር ኢንሼቲቭ ውጤት እያስገኘ ብዙዎችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል። በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ዜጎች የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ በማስቻል የስነ-ምግብ ስርዓት እንዲጎለብትም እንዲሁ። መርሃ ግብሩ በውጤታማነት ተጠናክሮ ከቀጠለባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች መካከል በአማራ ክልል ዋግ ኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ ይጠቀሳል፤ ዘርፉ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ሃብት ለማፍራት እያገዘ ነው። በዚህም ውጤታማ ከሆኑ የሰቆጣ ከተማ ነዋሪዎች ውስጥ ወጣት ዮናስ ደባሽ ይገኝበታል። ወጣቱ ለኢዜአ እንደገለጸው፤ በመርሀ ግብሩ በንብ ማነብ የጀመረውን ስራ በማሳደግ ወደ ዶሮ እርባታና መስኖ ልማት ተሸጋግሯል።   ወጣቱ ከንብ ማነብ ስራው በዓመት እስከ 200 ኪሎ ግራም የማር ምርት ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ አቅሙን ማሳደግ ችሏል። የንብ ማነብ ስራውን ከአካባቢ ጥበቃ ጋር ለማስተሳሰርም በሰቆጣ ከተማ በሚገኘው ተራራ ላይ ጥምር ጥቅም የሚሰጡ እጽዋትን እያለማ መሆኑን ይናገራል። አሁን ላይ ስራውን እያሳደገ በዶሮ እርባታው ዘርፍ በመሰማራትም ከራሱ አልፎ ለአካባቢው ገበያ መረጋጋት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በዶሮ እርባታው ዘርፍም ሦስት ሺህ ጫጩቶችን በማሳደግ ስራ የጀመረ ሲሆን አሁን ላይ ስምንት ሺህ የሁለት ወር የዶሮ ጫጩቶችን በማሳደግ ለአካባቢው ገበያ እያቀረበ እንደሚገኝም አንስቷል።   በዘርፉ ለ20 ሰዎች የስራ እድል መፍጠር የቻለው ወጣት ዮናስ፤ አሁን ላይ 20 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው ሃብት ማፍራት ችሏል። ወጣቱ ስራውንም ወደ ግብርና ኢንቨስትመንት ለማሳደግ ከከተማ አስተዳደሩ አንድ ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ተቀብሎ እያለማ መሆኑን ገልጿል። በወጣቱ የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወገኖች መካከል ወይዘሮ እህትወይ መለሰ በሰጡት አስተያየት፤ የወጣቱ ጥንካሬና ታታሪነት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።   እሳቸውም በዶሮ ጫጩት ማሳደጊያ ማዕከሉ በተፈጠረላቸው የስራ እድል በሚያገኙት የወር ገቢ ቤተሰቦቻቸውን ከማስተዳደር አልፈው ስለዶሮ እርባታ ልምድና እውቀት ማግኘት እንደቻሉ ተናግረዋል። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ አያሌው፤ በአስተዳደሩ የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ኢንሼቲቭ የሕብረተሰቡን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።   መርሀ ግብሩ ከምግብ ዋስትና ባለፈ አኮኖሚያዊ አቅምን ለማሳደግና ለስራ እድል አቅም እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል። የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ለወጣቶች የስራ እድል መፍጠር እንዲያስችል የብድርና የመስሪያ ቦታ ከማቅረብ ባለፈ ድጋፍና ክትትል ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ ወጣቶች የአንድ ቀን የዶሮ ጫጩት እያሳደጉ በማርባት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑንም ተናግረዋል።
ለወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በአማካይ 13 ነጥብ 9 በመቶ የስኳር ይዘት ያለው የሸንኮራ አገዳ እየቀረበ ነው
Dec 12, 2025 110
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 2/2018 (ኢዜአ)፡-ለወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በአማካይ 13 ነጥብ 9 በመቶ የስኳር ይዘት ያለው የሸንኮራ አገዳ እየቀረበ መሆኑ ተገልጿል። የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እዩኤል ለላንጎ፤ ሸንኮራ አገዳ ወደ ፋብሪካው የሚያጓጉዙ ማሽነሪዎች እና የፋብሪካው የጥገና ሥራ መጠናቀቁን ተከትሎ የማምረት ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል። በዚህም መሠረት ፋብሪካው የስኳር ምርት እያወጣ መሆኑን ሃላፊው ለኢዜአ ተናግረዋል።   ፋብሪካው በያዝነው በጀት ዓመት ሸንኮራ አገዳ ፈጭቶ በ21 ሠዓት ከ20 ደቂቃ ውስጥ ስኳር ማምረት መቻሉን ጠቁመዋል። ይህም በሀገራችን የስኳር ኢንዱስትሪ ታሪክ በአጭር ጊዜ የስኳር ምርት የተገኘበት ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል ብለዋል። ፋብሪካው በጥራት በመጠገኑ፣ ሸንኮራ አገዳው ጥራት ያለው እና አቅርቦቱም ባልተቆራረጠ ሁኔታ በመቅረቡ የተገኘ ውጤት ስለመሆኑም ተናግረዋል። የስኳር ምርት ለማውጣት ቀደም ሲል 78 ሠዓት፣ በ2016 ዓ.ም 30 ሠዓት እንዲሁም በ2017 ዓ.ም 28 ሠዓት ይፈጅ እንደነበርም አውስተዋል።   የሸንኮራ አገዳዎችን ዝርያ የማሻሻል፣ሸንኮራ አገዳ የመፍጨት፣ ስኳር የማምረት ዐቅምና የጨመቃ ሂደት ላይ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ሥራዎች በጥገና ወቅት መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። ለዘንድሮው ስኳር የማምረት ሥራ በአማካይ 13 ነጥብ 9 በመቶ የስኳር ይዘት ያለው የሸንኮራ አገዳ ለፋብሪካው እየቀረበ መሆኑንም አመላክተዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኮደርስ ስልጠና የመንግስት አገልግሎትን ለማዘመን አግዟል
Dec 12, 2025 44
አዶላ ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ የኮደርስ ስልጠና የመንግስት አገልግሎትን ለማዘመን እንዳገዛቸው የጉጂ ዞን የመንግስት ሰራተኞች ገለጹ፡፡ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከወሰዱ የአዶላ ከተማ የመንግስት ሰራተኞች መካከል ወጣት ጉደታ ገመዳ አንዱ ነው፡፡ ስልጠናው ራስን በቴክኖሎጂ በማብቃት ለደንበኞች የተቀላጠፈ አገልግሎትን ለመስጠት ተደማሪ አቅም እንደሚሆን ወጣት ገመዳ ተናግሯል።   ከስልጠናው የኮምፒውተር ሳይንስና የሰው ሰራሽ አስተውሎት እውቀትን ማግኘቱ ለስራው ስኬት እንዳገዘው ገልጿል። የወጣት ገመዳን ሀሳብ የሚጋራው ሌላው የከተማው የመንግስት ሰራተኛ ወጣት ደስታ ሀለኬ በበኩሉ ስልጠናው እውቀትና ቴክኖሎጂን በማቀናጀት ተወዳዳሪነቱን እንዳሳደገው ተናግሯል። ስልጠናውን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት መውሰዱን ገልፆ ስልጠናው የዜጎችን ብቃትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ ለተሻለ ስራ የሚያነሳሳ ነው ብሏል፡፡   ይህን እድል በመጠቀም የዘመነ አሰራር ለመተግበር በእውቀትና ክህሎት ለማበልጸግ ሁሉም ሰው ስልጠናውን በመውሰድ ለሀገር ልማት የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባም ልምዱን አካፍሏል፡፡ የዞኑ ሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት የሰው ሀብት ልማትና ስምሪት ቡድን መሪ አቶ ቢሉ ሶርሳ፤ የመንግስት ሰራተኞችን እውቀትና ክህሎት ለማሳደግ 25 ሺህ ሰራተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ መታቀዱን ገልጸዋል።   ስልጠናው የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑን ጠቁመው በእስካሁኑም 23 ሺህ 456 ሰራተኞች ስልጠናውን አጠናቀው የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ጠቁመዋል፡፡ ስልጠናው የመንግስት ሰራተኞችን ከቴክኖሎጂው ዓለም ጋር በማስተዋወቅ ብቁና ተወዳዳሪ የሚያደርግ አሰራርን እንዲከተሉ ማለሙን አክለዋል፡፡ ይህም በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፈጣንና መንግስታዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያግዝ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሠራሮችን አስቀርቷል
Dec 12, 2025 39
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 3/2018 (ኢዜአ)፡-መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሠራሮችን በመቅረፍ እርካታ በተሞላበት አግባብ አገልግሎቶች እንዲቀርቡ ማስቻሉ ተገለጸ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሥራት አዳሮ እንዳሉት፤ ማዕከሉ የተንዛዛና ለብልሹ አሠራር የተጋለጠውን የተቋማት አገልግሎት ከብልሹ አሠራር በፀዳ መልኩ ለማቅረብ አስችሏል። ተደራሽ አገልግሎት በመስጠት የዜጎችን እርካታ ማረጋገጥ እና ይባክን የነበረውን የሰው ኃይል፣ ጊዜ፣ ጉልበት ብሎም ሀብት ከብክነት ማዳኑንም ገልጸዋል። በክልሉ ከጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአንድ ማዕከል አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም አውስተዋል። አገልግሎቱ የተጀመረው በዘጠኝ ተቋማት በ28 አገልግሎት መሆኑን ገልጸው፤ አሁን ላይ አገልግሎቱ ወደ 35 ማደጉን አረጋግጠዋል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜም 3 ሺህ 641 ሰዎች አገልግሎቱን በአንድ ማዕከል ማግኘታቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በአምስት የዞንና የከተማ አሥተዳደሮች መሶብ የአንድ ማዕከልን ለማስፋፋት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል።
የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነትን ለመቀነስ...
Dec 12, 2025 92
በአብዛኛው ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑት የፋይናንስ ተቋማት እና ባንኮች መሆናቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር አስገነዘበ። በአስተዳደሩ የሳይበር መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መሀመድ ፈረጃ፤ የፋይናንስ ተቋማት፣ሚኒስቴሮች፣ የሕክምና ተቋማት፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ተቋማት፣ የጸጥታና ደኅንነት ተቋማት እንዲሁም ሚዲያዎች በተደጋጋሚ የጥቃት ዒላማ እንደሚደረጉም ተናግረዋል። ስለዚህም የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ቁልፍ የመሠረተ-ልማት ተቋማትን የሚመሩ አካላት ዘርፉን ወይም ተቋም ተኮር የሳይበር ደኅንነት ፖሊሲዎችን እና ፍሬም ወርኮችን መንደፍ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ከዚህም በተጨማሪ ስታንዳርዶችን እንዲቀርጹ እና አሠራሮች እንዲኖሯቸው ይጠበቃል ነው ያሉት። እነዚህን የአሠራር ሥርዓቶች ወደ መሬት ለማውረድ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል እና መሠረተ-ልማቱን ለመጠበቅ የሚያስችል ቴክኖሎጂ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል። በሰው፣ በአሠራር ሥርዓት እና በቴክኖሎጂ ተቋማት ራሳቸውን ዝግጁ ማድረግ እንዳለባቸውም መክረዋል። የሳይበር ደኅንነትን በተቋማት ለማረጋገጥ ዝቅተኛ የሚባሉትን የደኅንነት መስፈርቶች (Baseline) ማሟላት እና ተግባራዊነታቸውን መከታተል እንደሚጠበቅም አመላክተዋል። ይህንም ለማስቻልም መደበኛ የደኅንነት ዳሰሳና ኦዲት ማከናወን እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ጠንካራ የመከላከል ዐቅም ለመገንባት የ‘ዜሮ ትረስት’ መርኅን ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ይህ ማለትም ቀደም ሲል ስጋት ከውጭ እንጅ ከውስጥ የለም የሚል እንደነበር አውስተው፤ የ‘ዜሮ ትረስት’ መርኅ ግን “ማንንም አለማመን እና ሁሉንም ማረጋገጥ” በሚል የተመሰረት ሲሆን ይህም ስጋት ከውስጥም ከውጭም እንዳለ አምኖ መሥራት ነው ብለዋል። ከላይ ከተገለጹት ጥንቃቄዎች አልፎ የሳይበር ጥቃት ሊያጋጥም እንደሚችል እና የጥቃት ጉዳቱን ለመቀነስ እንዲሁም በጋራ ለመመከት እንዲቻል ከተቋማችን ጋር በቅርበት መሥራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። በአብዛኛው ጊዜ ለሳይበር ጥቃት ተጋላጭ የሆኑት የፋይናንስ ተቋማት እና ባንኮች መሆናቸውን ዓመታዊ የሳይበር ጥቃት ሪፖርታችን ያመለክታል ብለዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህዋ ሳይንስ ዲፕሎማሲ ማዕከል ለመሆን በቁርጠኝነት ትሰራለች 
Dec 11, 2025 71
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህዋ ሳይንስ ዲፕሎማሲ ማዕከል ለመሆንና ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደምትሰራ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት ከውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "ለሰላም፣ ለልማት እና ለጋራ ብልጽግና አህጉራዊ አጋርነትን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጁት አዲስ የህዋ ፎረም ተካሂዷል።   የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አብዲ ዘነበ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያን ህዋ ሳይንስ ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳደግ እየሰራ ነው። በፍጥነት እያደገ የመጣው የህዋ ሳይንስ በአገራት ልማት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑን አመልክተው፤ በተለይም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፣ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ፣ ለሳተላይት ኮሙኒኬሽንና ለሌሎች ስራዎች ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል።   በዓለም አቀፍ ደረጃ አፍሪካ በህዋ ሳይንስ ዲፕሎማሲ ያላት ውክልና በተቀናጀ መልኩ እንዲከናወን እንሰራለን ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከርና በስትራቴጂክ ዲፕሎማሲ ግንባር ቀደም ለመሆን ቁርጠኛ መሆኗንም ገልጸዋል። ፎረሙ አዲስ አበባን በህዋ ሳይንስ ዘርፍ የዲፕሎማሲ ማዕከል ለማድረግ ከሚከናወኑ ተግባራት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። በኢንስቲትዩቱ የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ ግዛቸው አሥራት (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በአፍሪካ የህዋ ሳይንስ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሰላም ግንባታና የብልጽግና ስራዎችን ለማጎልበት በጋራ እንሰራለን ብለዋል።   ዲፕሎማሲው በዓለም አቀፍ የህዋ ሳይንስ አስተዳደር የአፍሪካን ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ትብብርን ለማጠናከር፣ የተፈጥሮ ሀብቶችን ተደራሽነት ለማጠናከር እገዛ እንደሚያደርግም አብራርተዋል። በዘርፉ ምርምርና መረጃ ልውውጥ በማድረግ የአፍሪካን የጋራ አቅምና ቀጣናዊ ትብብር ማሳደግ እንደሚቻል ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የእውቀት፣ የቴክኒክና የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም ገልጸዋል። የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ይሽሩን አለማየሁ( ዶ/ር)፤ አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲና በመሆኗ ለህዋ ሳይንስ ዲፕሎማሲ ምቹ ናት ብለዋል።   አዲስ አበባን በዘርፉ የዲፕሎማሲ ማዕከል ማድረግ በዓለም አቀፍ መድረክ የኢትዮጵያንና የአፍሪካን አቅም ለማሳየት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የጂኦ ስፓሻልና ማኔጅመንት ተጠሪ አንድሬ ኖንጉርማ እንደተናገሩት፤ በህዋ ሳይንስ ዘርፍ የአፍሪካውያንን የጋራ ስራ ማጠናከር ያስፈልጋል።   ኢትዮጵያ በዘርፉ ውጤታማ ስራዎች እያከናወኑ ከሚገኙ አገራት አንዷ መሆኗን ጠቅሰው፤ በዘርፉ የመሪነት ሚና ለመወጣት የሚያስችል አቅም እንዳላት ተናግረዋል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 12ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል 
Dec 12, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 12ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ይደረጋሉ። ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከሲዳማ ቡና ይጫወታሉ። አርባምንጭ ከተማ በሊጉ በሊጉ ካከናወናቸው 11 ጨዋታዎች መካከል ሁለቱን ሲያሸንፍ ሰባት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪው ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ ሰባት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 20 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በስምንት ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና እስከ አሁን በሊጉ ባካሄዳቸው 10 ጨዋታዎች ሶስቱን ሲያሸንፍ በአራቱ ተሸንፏል። በሶስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። አራት ግቦችን በነዚህ ጨዋታዎች ከመረብ ላይ ሲያገናኝ 11 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ሲዳማ ቡና አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ12 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሃ ግብር ባህር ዳር ከተማ ከልደታ ክፍለ ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 11 ጨዋታዎች መካከል አንዱን ብቻ ያሸነፈው ባህር ዳር ከተማ በዘጠኝ ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። አንድ ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። አምስት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 16 ጎሎችን አስተናግዷል። ባህር ዳር ከተማ በአራት ነጥብ የመጨረሻውን 14ተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ልደታ ክፍለ ከተማ በሊጉ 11 ጨዋታዎችን አድርጎ አንድ ጊዜ ሲያሸንፍ ስምንት ጊዜ ተሸንፏል። ሁለት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ስምንት ግቦችን ሲያስቆጥር 22 ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በአምስት ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የዕለቱ የመጨረሻ መርሃ ግብር አዲስ አዳጊዎቹ ይርጋጨፌ ቡና እና ሸገር ከተማን ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ያገናኛል። ይርጋጨፌ ቡና በሊጉ ባደረጋቸው 11 ጨዋታዎች በሁለቱ ተሸንፎ በአምስቱ ተሸንፎ በአራቱ አቻ ወጥቷል። አራት ግቦችን ሲያስቆጥር 13 ግቦችን እሰተናግዷል። ቡድኑ በ10 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሸገር ከተማ በሊጉ ባከናወናቸው 10 ጨዋታዎች ሰባቱን ሲያሸንፍ ሶስት ጊዜ ተሸንፏል። በጨዋታዎቹ ላይ 16 ግቦችን ሲያስቆጥር 10 ግቦችን አስተናግዷል። ሸገር ከተማ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ21 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
የባህል ስፖርት ውድድሮች የህብረተሰቡን እሴቶች ለማስተዋወቅ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራሉ
Dec 11, 2025 82
ጅማ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ የባህል ስፖርታዊ ውድድሮች የህብረተሰቡን እሴቶች በማስተዋወቅ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥሩ የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ገለጹ። የጅማ ዞን የወረዳዎች የባህል ስፖርት ውድድርና እና ኤግዚቢሽን መርሀ ግብር ዛሬ መካሄድ ጀመረ።   በመክፈቻ መርሀግብሩ ላይ የተገኙት የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር እንዳሉት፤ በዞን ደረጃ የሚካሄደው የባህል ስፖርት ውድድርና የባህል ኤግዚቢሽን ማህበረሰባዊ እሴቶችን ሳይበረዙ ለትውልዱ ለማስተላለፍ መደላድል ፈጥሯል። ስፖርታዊ ውድድሩ የህብረተሰቡን ባህላዊ እሴቶች በማስተዋወቅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን ለማጉላት እንደሚያግዝም ጠቁመዋል።   በዞኑ ያሉትን የባህል እሴቶች ለማህበረሰባዊ ትስስር ለማዋል መሰል ኤግዚቢሽኖች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን አክለዋል። የጅማ ዞን ስፖርት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ነጉማ መኮንን በበኩላቸው፤ የባህል ስፖርት ውድድር የስፖርቱን ዘርፍ ወንድማማችነትና እህትማማችነት የሚያጠናክር መሆኑን ጠቁመዋል።   ለ13 ቀናት በሚካሄደው የባህል ስፖርት ውድድሩ ከ20 ወረዳዎችና ከአንድ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የባህል ስፖርት ተወዳዳሪዎችና የባህል ቡድኖች እንደሚሳተፉ ተናግረዋል። በአስር የባህል የስፖርት አይነቶች ውድድር የሚደረግ መሆኑን ገልጸው የፈረስ ግልቢያ፣ የገበጣ፣ቀስት፣ ትግል እና የገና ጨዋታ ስፖርቶች ይገኙባቸዋል ብለዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በክልሉ በመጪው ክረምት ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ችግኝ እየተዘጋጀ ነው
Dec 12, 2025 42
ባህርዳር ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በመጪው ክረምት ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ እየተዘጋጀ መሆኑ ተመላከተ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ እንደሀገር በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተራቁቱ መሬትን መልሶ በደን በመሸፈን እና የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ውሀ ሀብትን በማሳደግ ተጨባጭ ውጤት እያተመዘገበ ይገኛል። ባለፉት አመታት ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በትኩረት በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የክልሉን የደን ሽፋን ወደ 18 በመቶ ማሳደግ እንደተቻለም የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በተለያየ ምክንያት የተራቆተውን መሬት በደን መልሶ ለማልበስና የአየር ንብረት ሚዛኑን ለማስተካከል የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል።   ተግባሩን ለማስቀጠልም በመጪው ክረምት ለሚተከሉ‎ ችግኞች በመንግስት፣ በተቋማት፣ በማህበራትና በግል ተቋማት እንዲሁም ከ75 ሺህ በሚበልጡ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የተለያዩ ችግኞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል ብለዋል። ‎እስካሁንም በ65 ሺህ 694 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ፣ ሀገር በቀልና የውጭ ዝርያ ችግኞችን ለማዘጋጀት የችግኝ መደቦችን በማዘጋጀት ዘር ማፍሰስ መቻሉን ገልጸዋል። ‎ለአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተዘጋጁ ካሉት ችግኞችም 1 ነጥብ 7 ቢሊዮኑ በተራቆቱ፣ ለደን ተከላ በሚለዩና በበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ በሚከናወንባቸው ተፋሰሶች እንደሚተከሉም አስረድተዋል። ‎በክልሉ ባለፈው የክረምት ወቅት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተተከለው ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መካከል በመጀመሪያ ዙር በተካሄደ ቆጠራ 86 ነጥብ 3 በመቶው ፀድቆ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝም ታውቋል።
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ውጤታማ ናቸው
Dec 11, 2025 87
አዳማ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። የዘንድሮውን የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራን ስኬታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኙ የዘርፉ ሙያተኞችና የስራ ኃላፊዎችን ያሳተፈ የቅድመ ዝግጅት መድረክ በአዳማ ገልመ አባገዳ አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የቢሮው ኃላፊ ጌቱ ገመቹ በዚህ ወቅት እንደገለፁት ዘንድሮ የበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ዕቀባ ስራ በትኩረት ይከናወናል። በክልሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀው በዚህም የመሬት መራቆት፣ የአፈር መሸርሸር፣ የጎርፍና የድርቅ ስጋት መቀነሱን አስታውቀዋል። በተጨማሪም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራው የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ለመቋቋም፣ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ ዓምና የእርከን ማሰር፣ የአፈርና ውሃ ዕቀባ፣ የተፋሰስና በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራም የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ተግባር መከናወኑን አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ስራዎችም የከርሰ እና ገፀ ምድር የውሃ ሀብት እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመው የደረቁ ወንዞች፤ ጅረቶችና ሃይቆች መመለሳቸውን ተናግረዋል። በዚህም የበጋ መስኖ ስንዴን በበቂ የውሃ አቅርቦት ማልማት መቻሉን ገልጸው ለዓሣ ዕርባታና ለመጠጥ አገልግሎቶች እየዋሉ መሆኑንም ተናግረዋል። በተመሳሳይም ከሰውና እንስሳት ንኪኪ ነፃ ሆኖ ያገገመ መሬትን የደን ሀብቱን በመጠበቅ ለስራ ዕድል ፈጠራ ከማዋል ባለፈ ለንብ ማነብ ተግባር እየዋለ ይገኛል ብለዋል። በዘርፉ የተገኘውን ውጤት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ዘንድሮ የአፈርና ውሃ ዕቀባና የተፋሰስ ልማት ስራውን ለማከናወን ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። ለዚህም አምስት ሺህ 930 ተፋሰሶች መለየታቸውን ገልፀው በአፈርና ውሃ እቀባውና በተፋሰስ ልማት ስራው ዘጠኝ ነጥብ ስምንት ሚሊየን ህዝብን ለማሳተፍ በቂ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ-ግብር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በተግባር እያገዘ ይገኛል
Dec 11, 2025 121
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የከርሰ ምድር የውሃ አቅምን በማጎልበት የመስኖ እርሻዎች እንዲስፋፉ የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑም ተገልጿል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ተግባራዊ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክቷል፡፡ መርኃ-ግብሩ ለመጪው ትውልድ ተስፋ ብቻ ሳይሆን አሁን ያለውንም ትውልድ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ ሲሆን በስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አኳያ የራሱን ጉልህ ሚና እየተወጣ ነው፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ በብራዚል ቤለም በተካሄደው የዓለም የአየር ንብረት (COP-30) ጉባኤ ላይ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት (COP-32) ጉባኤን እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል። በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማትና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈጻሚ እና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የብሄራዊ ቴክኒክ ኮሚቴ ጸሃፊ ፋኑሴ መኮንን፤ የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እያደረገች ላለችው ጥረት ተግባራዊ ምላሽ እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን አርባ በመቶ የሚሆኑት ለምግብነት የሚውሉ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ አረንጓዴ አሻራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስና ለምነትን በመጨመር የግብርና ምርታማነት እንዲሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። የከርሰ ምድር የውሃ አቅምን በማሳደግ የመስኖ እርሻዎች እንዲስፋፉም የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት ለምግብነት አገልግሎት የሚውሉ አትክልትና ፍራፍሬዎችን ጨምሮ ሌሎች ችግኞች በስፋት የተተከሉ መሆናቸውን ጠቁመው፤ እነዚህም ለቤተሰብ የገቢ ምንጭና ለሥርዓተ ምግብ መሻሻልም ጉልህ ድርሻ ማበርከቱን ጠቅሰዋል፡፡ በአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር የተተከሉ ችግኞች ደን በመሆን ለማር ምርት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር የንብ አናቢዎችን ተጠቃሚነት እያሳደጉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በበርካታ ዘርፎች ሰፊ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር በተለይም የወጣቶችንና የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን እያሳደገ እንደሚገኝም አክለዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑና የተራቆቱ አካባቢዎች ወደ ምርታማነት እንዲለወጡ በማድረግ ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ የራሱን አስተዋጾኦ እያበረከተ መሆኑን አመላክተዋል፡፡      
በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ዕድልን ለማስፋፋት የግሉ ዘርፍ ሚና የጎላ ነው
Dec 10, 2025 144
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ዕድልን ለማስፋፋት የግሉ ዘርፍ ሚና የጎላ መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ”አረንጓዴ ስራዎች የተሻለ ነገ” በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ፎረምና ባዛር ማካሄድ ጀምሯል።   የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ መንግሥት በመደመር እሳቤ በኢኮኖሚ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልዱ ለማስረከብ በርካታ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል። ባለሃብቶችና ኢንተርፕራይዞች በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዙሪያ ያላቸውን ፈጠራና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያሳድጉ ፣ በተለይም በታዳሽ ሃይል ላይ የሚውል ካፒታል ፈሰስ ማድረግ፣ የኢኮኖሚ ኢኒሸቲቮችን ማገዝና ግብርናውን ማዘመን ላይ እንዲሳተፉ አሳስበዋል፡፡፡ ከነዚህ መካከል የሀገሪቱን የአየር ንብረት ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስራ ተጠቃሽ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግር በግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት፣ በአረንጓዴ ፈጠራ፣ ፋይናንስና ኢንተርፕርነርሺፕ ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ በአረንጓዴ የኢኮኖሚ ዘርፍ የሚፈጠር የስራ ዕድል ለኢትዮጵያ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ተግባሩ ከስራ፣ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ጋር ከተጣመረ ዘርፉን በፍጥነት ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚን በመጠቀም የስራ እድል ፈጠራን ለማስፋፋት የያዘቸውን ግብ እንድታሳካ አጋር አካላት የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።   በኢትዮጵያ የስዊድን ኤምባሲ ከፍተኛ የፕሮግራም ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኒኮላ ኤሪክሰን አረንጓዴ የስራ ዕድል ፈጠራ ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችውን ሽግግር ለማገዝና የማይበገርና የተሰባጠረ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ ታዳሽ የሃይል አቅርቦትና ትራንስፖርት፣የአየር ብክለት ልቀት ቅነሳ፣የቆሻሻ አወጋገድ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ በማደግ ላይ የሚገኙ አማራጮች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ይህንን እውን ማድረግ የሚችል በእውቀት የበለጸገና ጠንካራ ወጣት ሃይል አላት ብለዋል፡፡    
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 444
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል።   በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው።   አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 414
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 764
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 653
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ሐተታዎች
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 88
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል።   ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ።   ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡   የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።  
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 616
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 803
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 834
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 273
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2880
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2821
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3719
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2170
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1406
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7222
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5712
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58027
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52741
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33417
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30943
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26767
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25522
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25093
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25066
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58027
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52741
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33417
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30943
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 610
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው።   እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም።   የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል።   የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል።   ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!
ብልህ ከችግር ይማራል!!
Dec 2, 2025 401
ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል!! በማሙሽ ጋረደው ገራድ ተስፋዬ ተፈራ ትውልድና እድገታቸው በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ቃልሻ ቀበሌ ሲሆን በ1999 ዓ.ም በህገ ወጥ መንገድ ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው እንደነበር ያስታውሳሉ። ገንዘብ ለማግኘትና የመለውጥ ህልማቸውን ለማሳካት በሚል ሩቅ አስበው የጀመሩት ህገ ወጥ ጉዞ መዳረሻውን እስር ቤት አደረገው። ይህም ሁኔታ ''ሩቅ አሳቢ-ቅርብ አዳሪ'' አደረጋቸው። በባዕድ አገር በነበራቸው የ2 ዓመት የእስር ቤት ቆይታም የምግብ እጦትን ጨምሮ አካላዊ ጥቃትና ጉልበት ብዝበዛ እንዲሁም የተለያዩ ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶችን እንዳስተናገዱ ይናገራሉ።   ይህም አልበቃ ብሎ ከአካባቢው በህገወጥ መንገድ የሚሰደዱ ወጣቶችን ጉልበት በመጠቀም ሰፋፊ እርሻዎች ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ የጉልበት ብዝበዛ ይፈፀምባቸው እንደነበርም ያስታውሳሉ። ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል! የሚሉት ገራድ ተስፋዬ ሩቅ ሳይጓዙ፣ ገንዘብ ሳያወጡ ሰርተው መለወጥ የሚችሉበትን አካባቢያቸውን ፀጋ ሳያማትሩ ስደት መሄዳቸው ቁጭት ፈጥሮባቸው ነበር፡፡ ይህም በሀገራቸው እንኳንስ የለማን መሬት ይቅርና የተቦረቦረ መሬትን አልምቶ ጉልበትንና ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል ከእስር ቤት ቆይታቸው ተምረው ከእስር እንደተፈቱም ወዲያውኑ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል። በ2001 ዓ.ም ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሱም በማህበር ተደራጅተው ከመንግሥት ባገኙት 70 ሺህ ብር ብድር በእንስሳት እርባታ ላይ ለመሰማራት 4 የወተት ከብቶችን ገዝተው የእርባታ ስራ መጀመራቸውን ይገልጻሉ፡፡   በዚህም የዞኑ አስተዳደር የሰጣቸውን መሬት አልምተው የእንስሳት እርባታውን አስፋፍተው መስራት ጀመሩ፡፡ አሁን ላይ የወተት ላሞቹን ቁጥር 37 በማድረስ የወተት ምርታማነታቸው አድጎ ከቤት ፍጆታ አልፎ ለሆሳዕና ከተማና አካባቢው በቀን ከ670 ሊትር በላይ ወተት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ለ40 ወጣቶችም ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ከመፍጠራቸውም ባሻገር የተለያዩ የጭነትና የስራ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራት መቻላቸውን ይናገራሉ። የጀመሩትን ስራ በጥምር ግብርና የማስፋትና የሚያገኙትን ወተት በማቀነባበር ምርቱን በተለያየ መልኩ ለገበያ የማቅረብ ራዕይን ሰንቀው በትጋት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በህገወጥ ስደት ካጋጠማቸው ችግር ተነስተው በተግባር ያዩትን ለሌሎች በማስተማር የስደትን አስከፊነት ለአካባቢያቸው ወጣቶች እያስገነዘቡ መሆኑን ገልጸዋል።   ወጣቶች የስደትን አማራጭ ከመመልከታቸው በፊት የአካባቢያቸውን ፀጋ እንዲቃኙና ራዕይ ሰንቀው ራሳቸውን ለማሻሻል እንዲሰሩም መክረዋል። መለወጥ በውጪ ሀገር ብቻ ያለ የሚመስላቸው የቤተሰብ ኃላፊዎችም ልጆቻቸው በሀገራቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ በማመን ሊያግዟቸው እንደሚገባም አቶ ገራድ አስገንዝበዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደስላሴ፤ በክልሉ በርካታ ወጣቶች ያልተጨበጠ ተስፋ ሰንቀው ለህገወጥ ስደትና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡   በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ የሚያስችል አቅም በግብርናው ዘርፍ መኖሩን ጠቅሰው በዘርፉ የተሰማሩ ከስደት ተመላሾች በአካባቢያቸው ሰርተው ለስኬት እየበቁ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ላይ የሚገኙና የእነዚህን አካላት ተሞክሮ በመውሰድ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም