ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በሕገወጥ የነዳጅ ግብይት በተሰማሩ 562 ነዳጅ ማዳያዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል
Jul 3, 2025 89
አዲስ አበባ፤ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በሕገወጥ የነዳጅ ግብይት በመሰማራት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ችግር በፈጠሩ 562 የነዳጅ ማደያዎች ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ የነዳጅ ማዳያዎች፣ የነዳጅ አጓጓዦች እና ኩባንያዎች ጋር በዘርፉ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂዷል። በዚሁ ወቅት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) እንዳሉት በሕገወጥ መንገድ ሰውሰራሸ የነዳጅ እጥረት በመፍጠር ችግር እየፈጠሩ ባሉ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል። በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚገባው ነዳጅ ለዜጎች የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴና ለኢኮኖሚ ወሳኝ የመሆኑን ያህል ያለአግባብ ለመክበር በነዳጅ ላይ ሰው ሰራሽ የዋጋ ንረት የሚፈጥሩ አካላት መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ሚኒስቴሩ ባደረገው ክትትል በሕገወጥ የነዳጅ ግብይት ተሰማርተው ባገኛቸው 562 ነዳጅ ማዳያዎች ላይ የተለያየ ደረጃ ያለው አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን ጠቁመዋል። ከ222 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ቅጣት እንደተጣለባቸው ጠቅሰው፣ 54 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ሥር ውለው መጠየቃቸውንና በሕገወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ መወረሱንም አንስተዋል። በቀጣይ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የነዳጅ ስርጭት በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚተገበር ገልጸው፥ ሕግን አክብረው በመስራት የሀገር ባለውለታ የሆኑ ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል። በዚህም በሀገሪቱ ነዳጅ እያቀረቡ ባሉት 60 የነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የሚደረገው ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለፅ፥ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት የጋራ ስራዎች ይተገበራሉ ነው ያሉት። የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅ በበኩላቸው፥ በመዲናዋ የነዳጅ አቅርቦት ላይ በየቀኑ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በአግባቡ ሕዝቡን በማያገለግሉ አካላት እና ግብይቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማይፈጽሙት ላይ እየተወሰደ ያለው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በውይይቱ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች በበኩላቸው በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ቅንጅታዊ ሥራ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) በሰጡት ምላሽ፥ መንግሥት የነዳጅ ሪፎርም ካደረገ በኋላ በርካታ መሻሻሎች መኖራቸውን ገልጸዋል። ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የነዳጅ አቅርቦት በ10 በመቶ መጨመሩን ጠቅሰው፥ ከአቅርቦት ጋር የተያያዘ ችግር አለመኖሩን ጠቅሰዋል። ነዳጅ ማጓጓዝን በተመለከተ በቀጣይ በተሻለ ሁኔታ በባቡር በብዛት የማጓጓዝ፣ የመሰረተ ልማት ሁኔታዎችን የማሻሻል እና የዘርፉ ተዋናዮች የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች በዘላቂነት የመፍታት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ የጀመረው በረራ የኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር ያግዛል
Jul 3, 2025 63
አዲስ አበባ፤ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ የጀመረው በረራ ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተገለጸ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአገልግሎት ዘርፉ ከተመዘገቡ እድገቶች እና ውጤቶች መካከል አንዱ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሣምንት አራት ጊዜ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ ከተማ አዲስ በረራ ትናንት በይፋ አስጀምሯል። አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ ያደረገውን የመጀመሪያ የመንገደኞች በረራ አስመልክቶም ዛሬ በፖርቶ ከተማ የባለድርሻ አካላት የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የፓናል ውይይቱ በዋናነት የአየር መንገዱ የሚያደርገውን በረራ በኢኮኖሚያዊ ትስስር ይበልጥ ማጠናከር ላይ ያለመ ነው። በፓናል ውይይቱ ከተሳተፉት መካከል የፖርቶ አውሮፕላን ማረፊያ ዋና ዳይሬክተር ሩይ አልቬዝ፤ አየር መንገዱ የጀመረው በረራ ሁለቱ አገራትን በተለያዩ መስኮች ለማስተሳሰር እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የዛሬው የፓናል ውይይትም በረራውን በካርጎ አገልግሎት ለማስተሳሰር ያላቸውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ በውይይቱ በካርጎ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶችና ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውን ጠቅሰዋል። በፖርቶ አየር መንገድ ዋና የንግድ ኦፊሰር የሆኑት ካረን ስትራውጎ በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ የጀመረው በረራ አፍሪካን ብቻ ሳይሆን በስፔን በኩል አድርገን ከአውሮፓ ጋር ለመተሳሰር ያግዘናል ብለዋል። ፖርቶ የኢንዱስትሪ ከተማ መሆኗን አንስተው፤ ከዚህ አኳያ አየር መንገዱ የጀመረው በረራ ከኢኮኖሚ ትስስር አንጻር ትርጉም ያለው ለውጥ እንደሚያመጣ ያላቸውን እምነት ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፍጥነት እያደገ ያለ ስመጥር አየር መንገድ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የአውሮፕላን ቴክኖሎጂ ባለሙያ የሆኑት ጆን ጆርጅ ናቸው። የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለረዥም ጊዜ እንደሚያውቁት የሚናገሩት ጆን ጆርጅ፤ የአየር መንገዱ የፖርቶ በረራም ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በፖርቹጋል የሚኖሩ ዜጎች ወደ ተለያዩ ሀገራት በቀላሉ እንዲጓዙ እንደሚያስችል ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ በአገልግሎት ዘርፉ ከተመዘገቡ እድገቶች እና ውጤቶች መካከል አንዱ ማሳያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሆኑን አንስተዋል። አየር መንገዱ በተያዘው ዓመት ተጨማሪ 13 አውሮፕላኖችን በመግዛት አጠቃላይ የአውሮፕላን ብዛቱ 180 መድረሱን በመጠቆም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፤ ስድስት ተጨማሪ አዳዲስ መዳረሻዎችን በመጨመር አጠቃላይ ያላውን የመዳረሻ ብዛት ወደ 136 አሳድጓል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2035 ዓመታዊ ገቢውን ወደ 25 ቢሊየን ዶላር ከፍ ለማድረግና በዓመት 67 ሚሊዬን መንገደኞችን ለማጓጓዝ ራዕይ አስቀምጦ እየሰራ ይገኛል።
በክልሉ ለድህነት ቅነሳ ተግባራትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት ይሰጣል-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Jul 3, 2025 97
ሀዋሳ፤ ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል በድህነት ቅነሳ ተግባራት ላይ በማተኮር ገበያን ማረጋጋትና የሥራ ዕድል መፍጠር ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡ ክልሉ የተመሰረተበትን 5ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ክልሉ በአዲስ መልክ ከተደራጀ በኋላ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በዚህም የተመዘገቡ ስኬቶች እንዳሉ ገልጸው፣ የስኬቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ተሞክሮዎችን ማስፋት፣ ማነቆዎችን መፍታትና በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በቀጣይም ድህነትን በሚቀንሱ ተግባራት ላይ በማተኮር ገበያን ማረጋጋት፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠርና የቤተሰብ ብልጽግናን ማረጋገጥ የክልሉ መንግስት ትኩረቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። ለዚህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአቅርቦት እጥረት ችግርን በመፍታት የእያንዳንዱን ቤተሰብ ህይወት ለመቀየር የተቀረጸውን ፓኬጅ በመተግበር የህብረተሰቡን ገቢ ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል፡፡ በክልሉ ለወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር የተገኙ ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳደድሩ፣ በቀጣይ ተጨማሪ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ቀድመው ወደሥራ የገቡትን የመደገፍ ሥራ ይሰራል ብለዋል፡፡ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የተጀመሩ ሥራዎች እያስገኙ ያሉትን ውጤት በማስቀጠል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የህዝብን እርካታ ማረጋገጥ ሌላው ትኩረት መሆኑንም ጠቅሰዋል። በውይይት መድረኩ ከክልሉ መንግስት ዕቅድ ጋር የሚጣጣሙ ሀሳቦች መንጸባረቃቸውን ገልጸው፣ የክልሉን እድገት ለማፋጠን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። የክልሉን የአምስት ዓመታት ጉዞ ሰነድ ለውይይት ያቀረቡት የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በበኩላቸው በመሰረተ ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ሥራዎች ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ የሰጡ ናቸው ብለዋል። በዚህም ባለፉት አምስት ዓመታት ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ከ1 ሺህ 400 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። የክልሉን የመጠጥ ውሃ ሽፋኑን ወደ 64 በመቶ ያሳደጉ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውንም ተናግረዋል፡፡ በትምህርት ዘርፍም ቅድመ መደበኛ ላይ ትኩረት በማድረግ ባለሃብቱንና ህዝቡን በማስተባበር የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ መከናወኑን ገልጸው፣ በዚህም ከፍተኛ ለውጥ መታየቱንም ጠቁመዋል፡፡ አራርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት በግብርና፣ በእንስሳትና ዓሣ ሃብት ልማት ምርታማነትና ገቢን ለማሳደግ የተሰሩ ሥራዎችም በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ድርሻ አላቸው፡፡ የሲዳማ ክልል ከተደራጀ በኋላ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎችና በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ትናንት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተጎብኝተዋል። በዛሬው መድረክም በመስክ ምልከታ በታዩ ጉዳዮችና በቀረበው ሰነድ ላይ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በጋራ መክረዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ ነው - ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል
Jul 3, 2025 104
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ። ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል የዓለም አቀፉ ፖሊስ ድርጅት(ኢንተርፖል) ፕሬዚዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር አልራይዚን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው ውይት አድርገዋል። ውይይታቸው ኢትዮጵያና ኢንተርፖል ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል በኩል ትብብራቸውን ይበልጥ ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል። ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር ያከናወነቻቸው ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን በውይይታችን አንስተናል ብለዋል። ድንበር ዘለል ወንጀሎችን በጋራ በመከላከል ረገድ የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ እና የአቅም ግንባታ ትብብርን ለማስፋት የጋራ መግባባት መፈጠሩንም ተናግረዋል። የኢንተርፖል ፕሬዝዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ከኢንተርፖል ጋር ባላት ትብብር ውጤታማ እና ንቁ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑን አንስተዋል። ከውይይት በተጓዳኝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በለውጡ ያከናወናቸውን ዘመናዊ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎችንም ጎብኝተዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ ከ1958 ጀምሮ የኢንተርፖል አባል በመሆን በጋራ እየሰራች ነው።
በኢትዮጵያ የሰላም እና ጸጥታ ችግሮች ዋነኛ መንስኤ ስሁት የፖለቲካ ዕሳቤ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 3, 2025 71
አዲስ አበባ፤ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የሰላም እና ጸጥታ ችግሮች ዋነኛ መንስኤ ስሁት የሆነ የፖለቲካ ዕሳቤ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የሰላምና ጸጥታ ችግር አንደኛው ምክንያት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የስንፍና ፖለቲካ የወለደው ነው። በአገራችን የስንፍና ፖለቲካ ተንሰራፍቷል ብለዋል። በዚህ ምክንያት ግጭት ጠብ፣ተቃርኖን እየወለደ መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ አርሶ አደር፣ አርብቶ አደር፣ ላብ አደር አለ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አሁን ደግሞ አውርቶ አደር ተጨምሯል ብለዋል። እነዚህ ሰነፍ ፖለቲከኞች ስራ ሳይሰሩ፣ አገልግሎት ሳይሰጡ መብላት የሚፈልጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሌላኞቹ ክላሽ ካነገትኩ ፍላጎታቸውን የሚያሳኩ የሚመስላቸው እና በህዝብ የተመረጠን መንግስት በኃይልና በወሬ እናፈርሳለን ብለው የሚያምኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአንዳንድ አካባቢዎች ትምህርት አትማሩ፣ ማዳበሪያ አትውሰዱ ብለው ዜጎችን የሚገድሉ ሰዎች ካሉ ይህ እኩይ ዓላማ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ስትጋጭ ትርፍ እናገኛለን ብለው የሚያስቡ እሳት ጫሪ ጭልፊቶች አሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያውያንም እሳት ጫሪዎችን ማወቅና ማረም ያስፈልገናል፤ ያን ጊዜ ችግሩ ይፈታል ነው ያሉት። በአማራ ክልል የማህበረሰቡን የሰላም ሚና በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፥ ማህበረሰቡ የታጠቁ አካላትን አትግደሉ፣ አትግደሉልኝ፣ እናንተም አትሙቱልኝ ማለት አለበት ብለዋል። ልጆቼን ፈተና እንዳይፈተኑ እንዳይማሩ አትከልክሉ፣ እንዳንሰራ አታድርጉ፣ ማዳበሪያ እንዳይመጣ አታድርጉ ማለት አለበት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህንንም ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ የሰላም ፍላጎቱን አሳይቷል ብለዋል። በመሆኑም ለህዝብ ጥያቄ የከበረ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ማንኛውም ሰው ወደ ስልጣን ሲመጣ ከዚህ ቀደም ምን ሰርተህ ታውቃለህ፣ ግብር ከፍለሃል ወይ፣ ማንን አገለገልክ፣ ታማኝ ነህ ወይ ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል ብለዋል በማብራሪያቸው። ማህበረሰቡ የሰላምና የብልሹ አሰራር ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ሚናውን መወጣት እንዳለበት ገልጸው፤ ሰላም ሁል ጊዜ የሚገነባ ጉዳይ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ከዚህ ቀደም የተከሰቱ ግጭቶች ተፈትተው አንጻራዊ ሰላም መስፈኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ አንጻራዊ ሰላም ባይኖር ግብርናው፣ ማዕድኑ፣ ቱሪዝሙ አያድግም ነበር ሲሉ ጠቁመዋል። አሁንም ቀሪ ችግሮችን በመፍታትና በጋራ በመስራት የሰላምን ዘላቂነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። የትግራይ ክልልን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያም የፕሪቶሪያ ስምምንት የትግራይ ህዝብ ልጆቹን በየቀኑ ከማጣት ታድጓል ብለዋል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለሌሎች ሀገራት ደግሞ መንግስት ሰላም ይሻላል ብሎ ለተዋጉት ኃይሎች እድል ይሰጣል የሚል አዲስ ባህል መፍጠሩን ጠቁመዋል። በክልሉ አገልግሎትን በሚመለከት ቴሌኮም፣ ባንኮች፣ አየር መንገድና ሌሎችም አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ጀምረዋል ብለዋል። መንግስት ያልተመለሱ ተፋናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የጸና አቋም እንዳለው ገልጸዋል። የፌዴራል መንግስት ትግራይ ክልል ውስጥ ያሉ ጉዳዮችን በሰላም የመፍታት ፅኑ አቋሙን በተደጋጋሚ ማሳየቱን ገልጸው፤ የትግራይ ህዝብ ጦርነት ፈጽሞ አይፈልግም ሲሉ አብራርተዋል። ሆኖም የዓለምን ሁኔታና የዘመኑን ውጊያ ባለመገንዘብ፣ መንግስት በተለያዩ ችግሮች ተወሯል፤ የሚያግዙን ሀገራት አሉ በሚል የተሳሳተ ስሌት ጊዜው አሁን ነው በሚል ውጊያ ለመክፈት የሚፈልጉ መኖራቸውን ተናግረዋል። ይህ የተሳሳተ አካሄድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም፣ ችግሮችን በውይይት በንግግር መፍታት ነው ብለዋል። የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ወደ ጦርነት እንዳይገባ አሁኑኑ የሰላም ሚናችሁን ተወጡ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ ነው - ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል
Jul 3, 2025 104
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ። ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል የዓለም አቀፉ ፖሊስ ድርጅት(ኢንተርፖል) ፕሬዚዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር አልራይዚን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው ውይት አድርገዋል። ውይይታቸው ኢትዮጵያና ኢንተርፖል ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል በኩል ትብብራቸውን ይበልጥ ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል። ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር ያከናወነቻቸው ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን በውይይታችን አንስተናል ብለዋል። ድንበር ዘለል ወንጀሎችን በጋራ በመከላከል ረገድ የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ እና የአቅም ግንባታ ትብብርን ለማስፋት የጋራ መግባባት መፈጠሩንም ተናግረዋል። የኢንተርፖል ፕሬዝዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ከኢንተርፖል ጋር ባላት ትብብር ውጤታማ እና ንቁ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑን አንስተዋል። ከውይይት በተጓዳኝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በለውጡ ያከናወናቸውን ዘመናዊ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎችንም ጎብኝተዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ ከ1958 ጀምሮ የኢንተርፖል አባል በመሆን በጋራ እየሰራች ነው።
በኢትዮጵያ የሰላም እና ጸጥታ ችግሮች ዋነኛ መንስኤ ስሁት የፖለቲካ ዕሳቤ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 3, 2025 71
አዲስ አበባ፤ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የሰላም እና ጸጥታ ችግሮች ዋነኛ መንስኤ ስሁት የሆነ የፖለቲካ ዕሳቤ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የሰላምና ጸጥታ ችግር አንደኛው ምክንያት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የስንፍና ፖለቲካ የወለደው ነው። በአገራችን የስንፍና ፖለቲካ ተንሰራፍቷል ብለዋል። በዚህ ምክንያት ግጭት ጠብ፣ተቃርኖን እየወለደ መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ አርሶ አደር፣ አርብቶ አደር፣ ላብ አደር አለ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አሁን ደግሞ አውርቶ አደር ተጨምሯል ብለዋል። እነዚህ ሰነፍ ፖለቲከኞች ስራ ሳይሰሩ፣ አገልግሎት ሳይሰጡ መብላት የሚፈልጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሌላኞቹ ክላሽ ካነገትኩ ፍላጎታቸውን የሚያሳኩ የሚመስላቸው እና በህዝብ የተመረጠን መንግስት በኃይልና በወሬ እናፈርሳለን ብለው የሚያምኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአንዳንድ አካባቢዎች ትምህርት አትማሩ፣ ማዳበሪያ አትውሰዱ ብለው ዜጎችን የሚገድሉ ሰዎች ካሉ ይህ እኩይ ዓላማ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ስትጋጭ ትርፍ እናገኛለን ብለው የሚያስቡ እሳት ጫሪ ጭልፊቶች አሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያውያንም እሳት ጫሪዎችን ማወቅና ማረም ያስፈልገናል፤ ያን ጊዜ ችግሩ ይፈታል ነው ያሉት። በአማራ ክልል የማህበረሰቡን የሰላም ሚና በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፥ ማህበረሰቡ የታጠቁ አካላትን አትግደሉ፣ አትግደሉልኝ፣ እናንተም አትሙቱልኝ ማለት አለበት ብለዋል። ልጆቼን ፈተና እንዳይፈተኑ እንዳይማሩ አትከልክሉ፣ እንዳንሰራ አታድርጉ፣ ማዳበሪያ እንዳይመጣ አታድርጉ ማለት አለበት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህንንም ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ የሰላም ፍላጎቱን አሳይቷል ብለዋል። በመሆኑም ለህዝብ ጥያቄ የከበረ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ማንኛውም ሰው ወደ ስልጣን ሲመጣ ከዚህ ቀደም ምን ሰርተህ ታውቃለህ፣ ግብር ከፍለሃል ወይ፣ ማንን አገለገልክ፣ ታማኝ ነህ ወይ ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል ብለዋል በማብራሪያቸው። ማህበረሰቡ የሰላምና የብልሹ አሰራር ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ሚናውን መወጣት እንዳለበት ገልጸው፤ ሰላም ሁል ጊዜ የሚገነባ ጉዳይ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ከዚህ ቀደም የተከሰቱ ግጭቶች ተፈትተው አንጻራዊ ሰላም መስፈኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ አንጻራዊ ሰላም ባይኖር ግብርናው፣ ማዕድኑ፣ ቱሪዝሙ አያድግም ነበር ሲሉ ጠቁመዋል። አሁንም ቀሪ ችግሮችን በመፍታትና በጋራ በመስራት የሰላምን ዘላቂነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። የትግራይ ክልልን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያም የፕሪቶሪያ ስምምንት የትግራይ ህዝብ ልጆቹን በየቀኑ ከማጣት ታድጓል ብለዋል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለሌሎች ሀገራት ደግሞ መንግስት ሰላም ይሻላል ብሎ ለተዋጉት ኃይሎች እድል ይሰጣል የሚል አዲስ ባህል መፍጠሩን ጠቁመዋል። በክልሉ አገልግሎትን በሚመለከት ቴሌኮም፣ ባንኮች፣ አየር መንገድና ሌሎችም አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ጀምረዋል ብለዋል። መንግስት ያልተመለሱ ተፋናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የጸና አቋም እንዳለው ገልጸዋል። የፌዴራል መንግስት ትግራይ ክልል ውስጥ ያሉ ጉዳዮችን በሰላም የመፍታት ፅኑ አቋሙን በተደጋጋሚ ማሳየቱን ገልጸው፤ የትግራይ ህዝብ ጦርነት ፈጽሞ አይፈልግም ሲሉ አብራርተዋል። ሆኖም የዓለምን ሁኔታና የዘመኑን ውጊያ ባለመገንዘብ፣ መንግስት በተለያዩ ችግሮች ተወሯል፤ የሚያግዙን ሀገራት አሉ በሚል የተሳሳተ ስሌት ጊዜው አሁን ነው በሚል ውጊያ ለመክፈት የሚፈልጉ መኖራቸውን ተናግረዋል። ይህ የተሳሳተ አካሄድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም፣ ችግሮችን በውይይት በንግግር መፍታት ነው ብለዋል። የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ወደ ጦርነት እንዳይገባ አሁኑኑ የሰላም ሚናችሁን ተወጡ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያን ገናና ታሪክ በመጠበቅ ቴክኖሎጂን የታጠቀ በዕውቀት የሚመራ አስተማማኝ ሠራዊት የመገንባት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን
Jul 3, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ገናና ታሪክ በመጠበቅ ቴክኖሎጂን የታጠቀ በዕውቀት የሚመራ አስተማማኝ ሠራዊት የመገንባት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን ገለጹ። በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ ዋር ኮሌጅ የብሔራዊ ደኅንነት ኮንፍረንስ፣ የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ዋና የዘርፉ ተዋናዮች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል። የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአሸናፊነት አኩሪ ታሪክ የተጎናጸፈች ታላቅ ሀገር ናት ብለዋል። በኢትዮጵያ የሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደትም የሀገር መከላከያ ሠራዊት የከፈለው አኩri ታሪክም በትውልድ ሲዘከር የሚኖር በደማቅ አሻራ የተፃፈ መሆኑንም ገልጸዋል። የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲም የሀገር መከላከያ ሠራዊት ተቋማትን በተቀናጀ ሁኔታ ለመምራት ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል። የ21ኛ ክፍለ ዘመን የጦርነት ሁኔታ ተቀያሯል ያሉት ሌተናል ጄኔራል ይመር፥ የመከላከያ የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲም ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በማካተት መዘጋጀት ይኖርበታል ብለዋል። የኢትዮጵያን ገናና ታሪክ በመጠበቅ ቴክኖሎጂን የታጠቀ በዕውቀት የሚመራ አስተማማኝ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የመገንባት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የመከላከያ ምርምር ልማት ፖሊሲው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስና የሳይበር ጦርነት አዝማሚዎችን ታሳቢ ማድረግ የቴክኖሎጂ የውጊያ አውዶችን ማየት እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የመከላከደ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቡልቲ ታደሰ፥ የመከላከያ ሰራዊትን ሁለንተናዊ ለውጥ በስኬት መምራት የሚያስችሉ ጥናትና ምርምር ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የውስጥም ሆነ የውጭ ጠላት ሴራ በሩቅ መመከት የሚችል አስተማማኝ የጦር መሳሪያና ቴክኖሎጂ የታጠቀ ሰራዊት መገንባቱን አስታውቀዋል። በተመራማሪዎች የተዘጋጀው የመከላከያ ምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲም የሠራዊቱን የአሰራር ስርዓት በማዘመን የሠራዊቱን ሁለንተናዊ የማድረግ አቅም የሚያሳድግ መሆኑን አስረድተዋል። የመከላከያ ሠራዊት ተቋማት ወደ ስኬታማ የምርታማነት ምዕራፍ ተሸጋግረዋል ያሉት የኮሌጁ አዛዥ የመከላከያ ምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ሠራዊቱ የደረሰበትን ደረጃ በማላቅ የውስጥና የውጭ ጸረ ሰላም ኃሎች ሊቃጡት የሚችለውን ጥቃት መግታት በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱን እንስተዋል። በመከላከያ ዋር ኮሌጅ የስትራቴጂያዊ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዲን ሥራው ደማስ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ በመከላከያ ሰራዊት ተቋማት የሚያጋጥሙ ችግሮችንና መፍትሔዎቻቸውን የሚያትት ጥናትና ምርምር በማካሄድ ረቂቅ ፖሊሲው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በቀጣይ የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ሲገባ የሠራዊቱን ትጥቅ በራስ አቅም ከማሟላት ባለፈ ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የማይተካ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ኮሎኔል ሚኒሊክ ዋለ(ዶ/ር) ረቂቅ ፖሊሲው የመከላከያ ሠራዊት ተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር ማሰናሰል በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በዝግጅት ሂደትም ከሀገር ውስጥ ተቋማትና ሌሎች ሀገራት ልምድና ተሞክሮ ተቀምሮበት በመከለከያ ሠራዊት ተቋማት የሚያጋጥሙ ችግሮችን መፍትሔ መስጠት የሚያስች መሆኑን አስረድተዋል። የመከላከያ ሠራዊት ተቋማትም የሚሰሯቸውን የጥናትና ምርምር የልማት ስራዎች በተሻለ ጥራትና ፍጥነት ለማከናወን የተሻለ ግብዓት እንደሚሆን አንስተዋል። የምርምርና ልማት በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ተሞክሮ፣ የተገኙ ውጤቶችና ተግዳሮቶች እንዲሁም የኢፌዴሪ መከላከያ የምርምርና ልማት ፖሊሲ ረቂቅ ዝግጅት ሂደቶችን የሚዳስሱ የመነሻ ጽሁፎች ቀርበው ምክክር ተደርጎባቸዋል። የመድረኩ ተሳተፊዎችም በመከላከያ ዋር ኮሌጅ ቅጥር ግቢ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
የከተማዋን ሰላም ከማፅናቱ በተጓዳኝ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል
Jul 3, 2025 53
ባሕር ዳር፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፡- በባሕርዳር በበጀት ዓመቱ የከተማዋን ሰላም ከማፅናቱ በተጓዳኝ ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ። የከተማ አስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ ሥራዎች አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማና የቀጣይ 90 ቀናት ዕቅድ ላይ የመከረ መድረክ ዛሬ በባሕርዳር ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ጎሹ እንዳላማው እንደተናገሩት፤ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን ሰላም ከማፅናት ጎን ለጎን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ሥራዎችን በመፈጸም አበረታች ውጤት ተመዝግቧል። ይህም ከላይ እስከታች ያለው አመራር በመቀናጀት ሕብረተሰቡን በማስተባበርና በማሳተፍ የመጣ ነው ብለዋል። የባህር ዳርና አካባቢውን ሰላም ከማፅናት ባለፈ የኮሪደር ልማትን በማሳለጥ ፅዱ፣ አረንጓዴ፣ ለኑሮ የበለጠ የተመቸች፣ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ በትኩረት መሰራቱን አስታውቀዋል። በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን የተፈጥሮ ፀጋና ውበት ይበልጥ ጎልቶ እንዲወጣ ያስቻለ መሆኑን ጠቁመው፤ ሕዝቡ ለሰላሙ መከበርና ለልማቱ እየሰጠ ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል። በቀጣይ በየተቋማቱ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ አጠናክሮ የሕዝብን እርካታ ለማረጋገጥ የቀጣይ ትኩረታቸው እንደሆነም ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ጠቁመዋል። በብልፅግና ፓርቲ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን በበኩላቸው፤ በከተማዋ ሰላም እንዲሰፍንና የልማት ሥራዎች እንዲፋጠኑ ሕብረተሰቡን በማሳተፍ በተደረገው ጥረት ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። ሕብረተሰቡ ለከተማዋ ሰላም መጠበቅና ለልማት ስራዎች መፋጠን የበኩሉን መወጣቱን እንዲቀጥል አብሮ የመስራቱ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በባህርዳር ከተማ ዛሬ በተካሄደው መድረክ ላይም የከንቲባ ኮሚቴ አባላት፣ የክፍለ ከተማ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተባብረን ማደግ ነው የምንፈልገው የእኛን ፍላጎት ማክበርም ያስፈልጋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 3, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተባብረን ማደግ ነው የምንፈልገው የእኛን ፍላጎት ማክበርም ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናገሩ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በስብሰባው የመንግስትን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን የሰላምና የልማት ትብብር ማስቀጠል ፍላጎት አላት ብለዋል። ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የጎረቤት ሀገራት በጎ ምላሽ ሊሰጡ ይገባልም ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ሰላም የአካባቢው ሰላም ነው ያሉት ጠቅላይ መሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም ከሌለ የአካባቢ ሀገራትም ተጎጂ ይሆናሉ ሲሉ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከአካባቢው ሀገራት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ኢኮኖሚው እንዳይጎዳ ማድረግ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ሉዓላዊ ሀገር ናት የጎረቤቶቿንም ሉዓላዊነት ታከብራለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሀገራቱ ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ ለመኖርም የባሕር በር ፍላጎቷን ሰጥቶ በመቀበል መርሕ ሊያከብሩ እንደሚገባ አንስተዋል። ኢትዮጵያ 130 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት፣ የዘመነ ወታደርና ቴክኖሎጂ የታጠቀች ሀገር ብትሆንም በምንም አይነት ውጊያን አማራጭ አታደርግም ሲሉ ጠቅሰዋል። በመሆኑም ከሁሉም ወገን ጋር ያለውን ሰላማዊ ግንኙነት ለማስቀጠል ፍላጎት መኖሩንና ከሁሉም ወንድሞቻችን ጋር በሰላም መኖር እንፈልጋለን ብለዋል። ነገር ግን በሰላም የማያኖር ጉዳይ ሲኖር እራሳችንን ለመከላከል እንሞክራለን ሲሉም ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ መንግስት የፀና አቋም አለው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jul 3, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ መንግስት የፀና አቋም እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በስብሰባው የመንግስትን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ የፕሪቶሪያ ስምምነትን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ እንዳሉት ስምምነቱ ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል። ልጆቻቸውን በየቀኑ ከማጣት ታድጓል፤ ለኢትዮጵያ እና ለበርካታ ሀገራት ልምድ የሚሆን አዲስ የፖለቲካ ባህል አምጥቷል ብለዋል። አገልግሎትን በተመለከተ በወቅቱ ተቋርጠው የነበሩ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መጀመራቸውን ተናግረዋል። በክልሉ መንግስት የተቋቋመበት ሁኔታ ስምምነቱ ማመቻቸቱን ገልጸዋል። በራያና ፀለምት ያሉ ተፈናቃዮች ሙሉ በሙሉ መመለሳቸውን ጠቅሰው፤ ይህም የስምምነቱ ውጤት ነው ብለዋል። የወልቃይት ተፈናቃዮች የመመለስ ስራ መስራት እንዳለበት አንስተው፤ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ መንግስት የፀና አቋም እንዳለውም አረጋግጠዋል። ለዚህም በሁሉም ወገን ያሉ አካላት ተባባሪ መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የታጣቂዎች ተሃድሶ ተፈፃሚ መሆን እንዳለበትም ተናግረዋል። መንግስት በትግራይ ክልል ያለው ፍላጎት ልማት እና ልማት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልፀዋል። የትግራይ ሕዝብ ጦርነት ፈጽሞ አይፈልግም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሆኖም የዓለምን ሁኔታና የዘመኑን ውጊያ ባለመገንዘብ፣ መንግስት በተለያዩ ችግሮች ተወጥሯል፤ የሚያግዙን ሀገራት አሉ በሚል የተሳሳተ ስሌት ጊዜው አሁን ነው በሚል ውጊያ ለመክፈት የሚፈልጉ አሉ። ይህ የተሳሳተ አካሄድ ነው ብለዋል። ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም፣ ችግሮችን በውይይት፣ በንግግር መፍታት እንደሆነም ነው የተናገሩት። የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ወደ ጦርነት እንዳያመራ አሁኑኑ የሰላም ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። መንግስት አንድም ጥይት የመተኮስ ፍላጎት የለውም ፍላጎታችን ማልማት ነው ሲሉም አክለዋል።
የፕሪቶሪያ ስምምንት ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jul 3, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦የፕሪቶሪያ ስምምንት ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እያካሔደ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው። የትግራይ ክልልን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያም የፕሪቶሪያ ስምምንት የትግራይ ህዝብ ልጆቹን በየቀኑ ከማጣት ታድጓል ነው ያሉት። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለሌሎች ሀገራት ደግሞ መንግስት ሰላም ይሻላል ብሎ ለተዋጉት ኃይሎች እድል ይሰጣል የሚል አዲስ ባህል መፍጠሩን ጠቁመዋል። በክልሉ አገልግሎትን በሚመለከት ቴሌኮም፣ ባንኮች፣ አየር መንገድና ሌሎችም አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ጀምረዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የተፈናቀሉ ሰዎችን በሚመለከት ራያ መቶ በመቶ ጸለምትም ተመልሰዋል። ቀሪ ወልቃይት ያልተመለሱ አሉ፤ መንግስት ያልተመለሱ ተፋናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የጸና አቋም ነው ያለው ብለዋል። የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ ማቋቋምና ወደ ማህበረሰቡ መቀላቀልም በፍጥነት መፈጸም እንዳለበት ገልጸው፥ይህ ጥቅሙ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጭምር ነው ያሉት። የፌደራል መንግስት ትግራይ ክልል ውስጥ ያሉ ጉዳዮችን በሰላም የመፍታት ፅኑ አቋሙን በተደጋጋሚ ማሳየቱን ገልጸው፤የትግራይ ህዝብ ጦርነት ፈጽሞ አይፈልግም ሲሉ አብራርተዋል። ሆኖም የዓለምን ሁኔታና የዘመኑን ውጊያ ባለመገንዘብ፣ መንግስት በተለያዩ ችግሮች ተወሯል፤የሚያግዙን ሀገራት አሉ በሚል የተሳሳተ ስሌት ጊዜው አሁን ነው በሚል ውጊያ ለመክፈት የሚፈልጉ መኖራቸውን ተናግረዋል። ይህ የተሳሳተ አካሄድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም፣ ችገሮችን በውይይት በንግግር መፍታት ነው ብለዋል። የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ወደ ጦርነት እንዳይገባ አሁኑኑ የሰላም ሚናችሁን ተወጡ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። መንግስት አንድም ጥይት የመተኮስ ፍላጎት እንደሌለው በመጠቆም፥ሀገር ማልመት ነው ፍላጎታችን፤ ሁሉም ህዝብ ማወቅ ያለበት ጦርነት አያስፈልግም ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ትግራይ ክልልን ጨምሮ ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ሁሉም የበኩሉን ሚና ማበርከት አስፈላጊ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
በሰቆጣ ከተማ ሰላምን ከመጠበቅ ጎን ለጎን የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ጥያቄ ለመመለስ እየተሰራ ነው
Jul 3, 2025 69
ሰቆጣ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፡-በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ ሰላምን ከመጠበቅ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ በሰልፍ ላነሳው የልማት ተጠቃሚነት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ ለኢዜአ እንደገለጹት በከተማው ህብረተሰቡን ያሳተፈ የፀጥታ ሥራ በመሰራቱ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን ተችሏል። የተረጋገጠውን ሰላም በመጠቀም ህብረተሰቡ በህዝባዊ ሰልፍ የጠየቀውን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለእዚህም የከተማው ነዋሪዎች የረዥም ጊዜ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየው የሰቆጣ-ብልባላ-ላልይበላ-ጋሸና የአስፋልት መንገድ ሥራ በአሁኑ ወቅት መጀመሩ በማሳያነት ጠቅሰዋል። በተጨማሪም በከተማ አስተዳደሩ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የትምህርት፣ የጤና፣ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጠቀሜታ ያላቸው ከ19 በላይ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑን አስታውቀዋል። እየተገነቡ ያሉ መሰረተ ልማቶችን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ የከተማው ነዋሪዎች በህዝባዊ ሰልፍ ላነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት አስተዳደሩ የጀመረውን ጥረት እንደሚያጠናክርም አረጋግጠዋል። ከእዚህ በተጨማሪ የከተማ አስተዳደሩ አመራር የህዝቡን ፍላጎትና ጥያቄ መሰረት ያደረገ እቅድ በማውጣት ተጨማሪ የልማት ስራዎችን ለማከናወን ይሰራል ብለዋል። የሰላምና የልማት ሥራዎች ለመንግስት ብቻ የሚተው ባለመሆናቸው በየአካባቢው ህብረተሰቡን ያሳተፉ የልማት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ምክትል ከንቲባው አረጋግጠዋል። "ህዝቡ ፍላጎቱ ሰላምና ልማት እንደሆነ በሰላማዊ ሰልፍ ደጋግሞ ጠይቋል" ያሉት አቶ ጌትነት፣ በጫካ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ሀይሎችም የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው እንዲመጡ ህዝቡ የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል። የሰቆጣ ከተማ ነዋሪዎች ባለፈው እሁድ ሰላምና ልማትን የሚደግፍ እና ጽንፈኝነትን የሚያወግዝ ህዝባዊ ሰልፍ ማካሄዳቸው የሚታወስ ነው።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ ነው - ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል
Jul 3, 2025 104
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ። ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል የዓለም አቀፉ ፖሊስ ድርጅት(ኢንተርፖል) ፕሬዚዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር አልራይዚን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው ውይት አድርገዋል። ውይይታቸው ኢትዮጵያና ኢንተርፖል ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል በኩል ትብብራቸውን ይበልጥ ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል። ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር ያከናወነቻቸው ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን በውይይታችን አንስተናል ብለዋል። ድንበር ዘለል ወንጀሎችን በጋራ በመከላከል ረገድ የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ እና የአቅም ግንባታ ትብብርን ለማስፋት የጋራ መግባባት መፈጠሩንም ተናግረዋል። የኢንተርፖል ፕሬዝዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ከኢንተርፖል ጋር ባላት ትብብር ውጤታማ እና ንቁ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑን አንስተዋል። ከውይይት በተጓዳኝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በለውጡ ያከናወናቸውን ዘመናዊ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎችንም ጎብኝተዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ ከ1958 ጀምሮ የኢንተርፖል አባል በመሆን በጋራ እየሰራች ነው።
በኢትዮጵያ የሰላም እና ጸጥታ ችግሮች ዋነኛ መንስኤ ስሁት የፖለቲካ ዕሳቤ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 3, 2025 71
አዲስ አበባ፤ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የሰላም እና ጸጥታ ችግሮች ዋነኛ መንስኤ ስሁት የሆነ የፖለቲካ ዕሳቤ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የሰላምና ጸጥታ ችግር አንደኛው ምክንያት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የስንፍና ፖለቲካ የወለደው ነው። በአገራችን የስንፍና ፖለቲካ ተንሰራፍቷል ብለዋል። በዚህ ምክንያት ግጭት ጠብ፣ተቃርኖን እየወለደ መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ አርሶ አደር፣ አርብቶ አደር፣ ላብ አደር አለ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አሁን ደግሞ አውርቶ አደር ተጨምሯል ብለዋል። እነዚህ ሰነፍ ፖለቲከኞች ስራ ሳይሰሩ፣ አገልግሎት ሳይሰጡ መብላት የሚፈልጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሌላኞቹ ክላሽ ካነገትኩ ፍላጎታቸውን የሚያሳኩ የሚመስላቸው እና በህዝብ የተመረጠን መንግስት በኃይልና በወሬ እናፈርሳለን ብለው የሚያምኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአንዳንድ አካባቢዎች ትምህርት አትማሩ፣ ማዳበሪያ አትውሰዱ ብለው ዜጎችን የሚገድሉ ሰዎች ካሉ ይህ እኩይ ዓላማ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ስትጋጭ ትርፍ እናገኛለን ብለው የሚያስቡ እሳት ጫሪ ጭልፊቶች አሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያውያንም እሳት ጫሪዎችን ማወቅና ማረም ያስፈልገናል፤ ያን ጊዜ ችግሩ ይፈታል ነው ያሉት። በአማራ ክልል የማህበረሰቡን የሰላም ሚና በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፥ ማህበረሰቡ የታጠቁ አካላትን አትግደሉ፣ አትግደሉልኝ፣ እናንተም አትሙቱልኝ ማለት አለበት ብለዋል። ልጆቼን ፈተና እንዳይፈተኑ እንዳይማሩ አትከልክሉ፣ እንዳንሰራ አታድርጉ፣ ማዳበሪያ እንዳይመጣ አታድርጉ ማለት አለበት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህንንም ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ የሰላም ፍላጎቱን አሳይቷል ብለዋል። በመሆኑም ለህዝብ ጥያቄ የከበረ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ማንኛውም ሰው ወደ ስልጣን ሲመጣ ከዚህ ቀደም ምን ሰርተህ ታውቃለህ፣ ግብር ከፍለሃል ወይ፣ ማንን አገለገልክ፣ ታማኝ ነህ ወይ ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል ብለዋል በማብራሪያቸው። ማህበረሰቡ የሰላምና የብልሹ አሰራር ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ሚናውን መወጣት እንዳለበት ገልጸው፤ ሰላም ሁል ጊዜ የሚገነባ ጉዳይ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ከዚህ ቀደም የተከሰቱ ግጭቶች ተፈትተው አንጻራዊ ሰላም መስፈኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ አንጻራዊ ሰላም ባይኖር ግብርናው፣ ማዕድኑ፣ ቱሪዝሙ አያድግም ነበር ሲሉ ጠቁመዋል። አሁንም ቀሪ ችግሮችን በመፍታትና በጋራ በመስራት የሰላምን ዘላቂነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። የትግራይ ክልልን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያም የፕሪቶሪያ ስምምንት የትግራይ ህዝብ ልጆቹን በየቀኑ ከማጣት ታድጓል ብለዋል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለሌሎች ሀገራት ደግሞ መንግስት ሰላም ይሻላል ብሎ ለተዋጉት ኃይሎች እድል ይሰጣል የሚል አዲስ ባህል መፍጠሩን ጠቁመዋል። በክልሉ አገልግሎትን በሚመለከት ቴሌኮም፣ ባንኮች፣ አየር መንገድና ሌሎችም አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ጀምረዋል ብለዋል። መንግስት ያልተመለሱ ተፋናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የጸና አቋም እንዳለው ገልጸዋል። የፌዴራል መንግስት ትግራይ ክልል ውስጥ ያሉ ጉዳዮችን በሰላም የመፍታት ፅኑ አቋሙን በተደጋጋሚ ማሳየቱን ገልጸው፤ የትግራይ ህዝብ ጦርነት ፈጽሞ አይፈልግም ሲሉ አብራርተዋል። ሆኖም የዓለምን ሁኔታና የዘመኑን ውጊያ ባለመገንዘብ፣ መንግስት በተለያዩ ችግሮች ተወሯል፤ የሚያግዙን ሀገራት አሉ በሚል የተሳሳተ ስሌት ጊዜው አሁን ነው በሚል ውጊያ ለመክፈት የሚፈልጉ መኖራቸውን ተናግረዋል። ይህ የተሳሳተ አካሄድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም፣ ችግሮችን በውይይት በንግግር መፍታት ነው ብለዋል። የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ወደ ጦርነት እንዳይገባ አሁኑኑ የሰላም ሚናችሁን ተወጡ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያን ገናና ታሪክ በመጠበቅ ቴክኖሎጂን የታጠቀ በዕውቀት የሚመራ አስተማማኝ ሠራዊት የመገንባት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን
Jul 3, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ገናና ታሪክ በመጠበቅ ቴክኖሎጂን የታጠቀ በዕውቀት የሚመራ አስተማማኝ ሠራዊት የመገንባት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን ገለጹ። በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ ዋር ኮሌጅ የብሔራዊ ደኅንነት ኮንፍረንስ፣ የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ዋና የዘርፉ ተዋናዮች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል። የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአሸናፊነት አኩሪ ታሪክ የተጎናጸፈች ታላቅ ሀገር ናት ብለዋል። በኢትዮጵያ የሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደትም የሀገር መከላከያ ሠራዊት የከፈለው አኩri ታሪክም በትውልድ ሲዘከር የሚኖር በደማቅ አሻራ የተፃፈ መሆኑንም ገልጸዋል። የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲም የሀገር መከላከያ ሠራዊት ተቋማትን በተቀናጀ ሁኔታ ለመምራት ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል። የ21ኛ ክፍለ ዘመን የጦርነት ሁኔታ ተቀያሯል ያሉት ሌተናል ጄኔራል ይመር፥ የመከላከያ የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲም ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በማካተት መዘጋጀት ይኖርበታል ብለዋል። የኢትዮጵያን ገናና ታሪክ በመጠበቅ ቴክኖሎጂን የታጠቀ በዕውቀት የሚመራ አስተማማኝ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የመገንባት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የመከላከያ ምርምር ልማት ፖሊሲው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስና የሳይበር ጦርነት አዝማሚዎችን ታሳቢ ማድረግ የቴክኖሎጂ የውጊያ አውዶችን ማየት እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የመከላከደ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቡልቲ ታደሰ፥ የመከላከያ ሰራዊትን ሁለንተናዊ ለውጥ በስኬት መምራት የሚያስችሉ ጥናትና ምርምር ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የውስጥም ሆነ የውጭ ጠላት ሴራ በሩቅ መመከት የሚችል አስተማማኝ የጦር መሳሪያና ቴክኖሎጂ የታጠቀ ሰራዊት መገንባቱን አስታውቀዋል። በተመራማሪዎች የተዘጋጀው የመከላከያ ምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲም የሠራዊቱን የአሰራር ስርዓት በማዘመን የሠራዊቱን ሁለንተናዊ የማድረግ አቅም የሚያሳድግ መሆኑን አስረድተዋል። የመከላከያ ሠራዊት ተቋማት ወደ ስኬታማ የምርታማነት ምዕራፍ ተሸጋግረዋል ያሉት የኮሌጁ አዛዥ የመከላከያ ምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ሠራዊቱ የደረሰበትን ደረጃ በማላቅ የውስጥና የውጭ ጸረ ሰላም ኃሎች ሊቃጡት የሚችለውን ጥቃት መግታት በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱን እንስተዋል። በመከላከያ ዋር ኮሌጅ የስትራቴጂያዊ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዲን ሥራው ደማስ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ በመከላከያ ሰራዊት ተቋማት የሚያጋጥሙ ችግሮችንና መፍትሔዎቻቸውን የሚያትት ጥናትና ምርምር በማካሄድ ረቂቅ ፖሊሲው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በቀጣይ የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ሲገባ የሠራዊቱን ትጥቅ በራስ አቅም ከማሟላት ባለፈ ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የማይተካ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ኮሎኔል ሚኒሊክ ዋለ(ዶ/ር) ረቂቅ ፖሊሲው የመከላከያ ሠራዊት ተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር ማሰናሰል በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በዝግጅት ሂደትም ከሀገር ውስጥ ተቋማትና ሌሎች ሀገራት ልምድና ተሞክሮ ተቀምሮበት በመከለከያ ሠራዊት ተቋማት የሚያጋጥሙ ችግሮችን መፍትሔ መስጠት የሚያስች መሆኑን አስረድተዋል። የመከላከያ ሠራዊት ተቋማትም የሚሰሯቸውን የጥናትና ምርምር የልማት ስራዎች በተሻለ ጥራትና ፍጥነት ለማከናወን የተሻለ ግብዓት እንደሚሆን አንስተዋል። የምርምርና ልማት በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ተሞክሮ፣ የተገኙ ውጤቶችና ተግዳሮቶች እንዲሁም የኢፌዴሪ መከላከያ የምርምርና ልማት ፖሊሲ ረቂቅ ዝግጅት ሂደቶችን የሚዳስሱ የመነሻ ጽሁፎች ቀርበው ምክክር ተደርጎባቸዋል። የመድረኩ ተሳተፊዎችም በመከላከያ ዋር ኮሌጅ ቅጥር ግቢ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
የከተማዋን ሰላም ከማፅናቱ በተጓዳኝ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል
Jul 3, 2025 53
ባሕር ዳር፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፡- በባሕርዳር በበጀት ዓመቱ የከተማዋን ሰላም ከማፅናቱ በተጓዳኝ ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ። የከተማ አስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ ሥራዎች አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማና የቀጣይ 90 ቀናት ዕቅድ ላይ የመከረ መድረክ ዛሬ በባሕርዳር ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ጎሹ እንዳላማው እንደተናገሩት፤ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን ሰላም ከማፅናት ጎን ለጎን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ሥራዎችን በመፈጸም አበረታች ውጤት ተመዝግቧል። ይህም ከላይ እስከታች ያለው አመራር በመቀናጀት ሕብረተሰቡን በማስተባበርና በማሳተፍ የመጣ ነው ብለዋል። የባህር ዳርና አካባቢውን ሰላም ከማፅናት ባለፈ የኮሪደር ልማትን በማሳለጥ ፅዱ፣ አረንጓዴ፣ ለኑሮ የበለጠ የተመቸች፣ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ በትኩረት መሰራቱን አስታውቀዋል። በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን የተፈጥሮ ፀጋና ውበት ይበልጥ ጎልቶ እንዲወጣ ያስቻለ መሆኑን ጠቁመው፤ ሕዝቡ ለሰላሙ መከበርና ለልማቱ እየሰጠ ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል። በቀጣይ በየተቋማቱ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ አጠናክሮ የሕዝብን እርካታ ለማረጋገጥ የቀጣይ ትኩረታቸው እንደሆነም ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ጠቁመዋል። በብልፅግና ፓርቲ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን በበኩላቸው፤ በከተማዋ ሰላም እንዲሰፍንና የልማት ሥራዎች እንዲፋጠኑ ሕብረተሰቡን በማሳተፍ በተደረገው ጥረት ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። ሕብረተሰቡ ለከተማዋ ሰላም መጠበቅና ለልማት ስራዎች መፋጠን የበኩሉን መወጣቱን እንዲቀጥል አብሮ የመስራቱ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በባህርዳር ከተማ ዛሬ በተካሄደው መድረክ ላይም የከንቲባ ኮሚቴ አባላት፣ የክፍለ ከተማ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተባብረን ማደግ ነው የምንፈልገው የእኛን ፍላጎት ማክበርም ያስፈልጋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 3, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተባብረን ማደግ ነው የምንፈልገው የእኛን ፍላጎት ማክበርም ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናገሩ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በስብሰባው የመንግስትን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን የሰላምና የልማት ትብብር ማስቀጠል ፍላጎት አላት ብለዋል። ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የጎረቤት ሀገራት በጎ ምላሽ ሊሰጡ ይገባልም ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ሰላም የአካባቢው ሰላም ነው ያሉት ጠቅላይ መሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም ከሌለ የአካባቢ ሀገራትም ተጎጂ ይሆናሉ ሲሉ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከአካባቢው ሀገራት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ኢኮኖሚው እንዳይጎዳ ማድረግ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ሉዓላዊ ሀገር ናት የጎረቤቶቿንም ሉዓላዊነት ታከብራለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሀገራቱ ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ ለመኖርም የባሕር በር ፍላጎቷን ሰጥቶ በመቀበል መርሕ ሊያከብሩ እንደሚገባ አንስተዋል። ኢትዮጵያ 130 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት፣ የዘመነ ወታደርና ቴክኖሎጂ የታጠቀች ሀገር ብትሆንም በምንም አይነት ውጊያን አማራጭ አታደርግም ሲሉ ጠቅሰዋል። በመሆኑም ከሁሉም ወገን ጋር ያለውን ሰላማዊ ግንኙነት ለማስቀጠል ፍላጎት መኖሩንና ከሁሉም ወንድሞቻችን ጋር በሰላም መኖር እንፈልጋለን ብለዋል። ነገር ግን በሰላም የማያኖር ጉዳይ ሲኖር እራሳችንን ለመከላከል እንሞክራለን ሲሉም ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ መንግስት የፀና አቋም አለው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jul 3, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ መንግስት የፀና አቋም እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በስብሰባው የመንግስትን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ የፕሪቶሪያ ስምምነትን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ እንዳሉት ስምምነቱ ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል። ልጆቻቸውን በየቀኑ ከማጣት ታድጓል፤ ለኢትዮጵያ እና ለበርካታ ሀገራት ልምድ የሚሆን አዲስ የፖለቲካ ባህል አምጥቷል ብለዋል። አገልግሎትን በተመለከተ በወቅቱ ተቋርጠው የነበሩ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መጀመራቸውን ተናግረዋል። በክልሉ መንግስት የተቋቋመበት ሁኔታ ስምምነቱ ማመቻቸቱን ገልጸዋል። በራያና ፀለምት ያሉ ተፈናቃዮች ሙሉ በሙሉ መመለሳቸውን ጠቅሰው፤ ይህም የስምምነቱ ውጤት ነው ብለዋል። የወልቃይት ተፈናቃዮች የመመለስ ስራ መስራት እንዳለበት አንስተው፤ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ መንግስት የፀና አቋም እንዳለውም አረጋግጠዋል። ለዚህም በሁሉም ወገን ያሉ አካላት ተባባሪ መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የታጣቂዎች ተሃድሶ ተፈፃሚ መሆን እንዳለበትም ተናግረዋል። መንግስት በትግራይ ክልል ያለው ፍላጎት ልማት እና ልማት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልፀዋል። የትግራይ ሕዝብ ጦርነት ፈጽሞ አይፈልግም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሆኖም የዓለምን ሁኔታና የዘመኑን ውጊያ ባለመገንዘብ፣ መንግስት በተለያዩ ችግሮች ተወጥሯል፤ የሚያግዙን ሀገራት አሉ በሚል የተሳሳተ ስሌት ጊዜው አሁን ነው በሚል ውጊያ ለመክፈት የሚፈልጉ አሉ። ይህ የተሳሳተ አካሄድ ነው ብለዋል። ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም፣ ችግሮችን በውይይት፣ በንግግር መፍታት እንደሆነም ነው የተናገሩት። የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ወደ ጦርነት እንዳያመራ አሁኑኑ የሰላም ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። መንግስት አንድም ጥይት የመተኮስ ፍላጎት የለውም ፍላጎታችን ማልማት ነው ሲሉም አክለዋል።
የፕሪቶሪያ ስምምንት ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jul 3, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦የፕሪቶሪያ ስምምንት ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እያካሔደ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው። የትግራይ ክልልን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያም የፕሪቶሪያ ስምምንት የትግራይ ህዝብ ልጆቹን በየቀኑ ከማጣት ታድጓል ነው ያሉት። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለሌሎች ሀገራት ደግሞ መንግስት ሰላም ይሻላል ብሎ ለተዋጉት ኃይሎች እድል ይሰጣል የሚል አዲስ ባህል መፍጠሩን ጠቁመዋል። በክልሉ አገልግሎትን በሚመለከት ቴሌኮም፣ ባንኮች፣ አየር መንገድና ሌሎችም አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ጀምረዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የተፈናቀሉ ሰዎችን በሚመለከት ራያ መቶ በመቶ ጸለምትም ተመልሰዋል። ቀሪ ወልቃይት ያልተመለሱ አሉ፤ መንግስት ያልተመለሱ ተፋናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የጸና አቋም ነው ያለው ብለዋል። የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ ማቋቋምና ወደ ማህበረሰቡ መቀላቀልም በፍጥነት መፈጸም እንዳለበት ገልጸው፥ይህ ጥቅሙ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጭምር ነው ያሉት። የፌደራል መንግስት ትግራይ ክልል ውስጥ ያሉ ጉዳዮችን በሰላም የመፍታት ፅኑ አቋሙን በተደጋጋሚ ማሳየቱን ገልጸው፤የትግራይ ህዝብ ጦርነት ፈጽሞ አይፈልግም ሲሉ አብራርተዋል። ሆኖም የዓለምን ሁኔታና የዘመኑን ውጊያ ባለመገንዘብ፣ መንግስት በተለያዩ ችግሮች ተወሯል፤የሚያግዙን ሀገራት አሉ በሚል የተሳሳተ ስሌት ጊዜው አሁን ነው በሚል ውጊያ ለመክፈት የሚፈልጉ መኖራቸውን ተናግረዋል። ይህ የተሳሳተ አካሄድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም፣ ችገሮችን በውይይት በንግግር መፍታት ነው ብለዋል። የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ ወደ ጦርነት እንዳይገባ አሁኑኑ የሰላም ሚናችሁን ተወጡ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። መንግስት አንድም ጥይት የመተኮስ ፍላጎት እንደሌለው በመጠቆም፥ሀገር ማልመት ነው ፍላጎታችን፤ ሁሉም ህዝብ ማወቅ ያለበት ጦርነት አያስፈልግም ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ትግራይ ክልልን ጨምሮ ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ሁሉም የበኩሉን ሚና ማበርከት አስፈላጊ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
በሰቆጣ ከተማ ሰላምን ከመጠበቅ ጎን ለጎን የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ጥያቄ ለመመለስ እየተሰራ ነው
Jul 3, 2025 69
ሰቆጣ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፡-በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ ሰላምን ከመጠበቅ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ በሰልፍ ላነሳው የልማት ተጠቃሚነት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ ለኢዜአ እንደገለጹት በከተማው ህብረተሰቡን ያሳተፈ የፀጥታ ሥራ በመሰራቱ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን ተችሏል። የተረጋገጠውን ሰላም በመጠቀም ህብረተሰቡ በህዝባዊ ሰልፍ የጠየቀውን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለእዚህም የከተማው ነዋሪዎች የረዥም ጊዜ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየው የሰቆጣ-ብልባላ-ላልይበላ-ጋሸና የአስፋልት መንገድ ሥራ በአሁኑ ወቅት መጀመሩ በማሳያነት ጠቅሰዋል። በተጨማሪም በከተማ አስተዳደሩ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የትምህርት፣ የጤና፣ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጠቀሜታ ያላቸው ከ19 በላይ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑን አስታውቀዋል። እየተገነቡ ያሉ መሰረተ ልማቶችን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ የከተማው ነዋሪዎች በህዝባዊ ሰልፍ ላነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት አስተዳደሩ የጀመረውን ጥረት እንደሚያጠናክርም አረጋግጠዋል። ከእዚህ በተጨማሪ የከተማ አስተዳደሩ አመራር የህዝቡን ፍላጎትና ጥያቄ መሰረት ያደረገ እቅድ በማውጣት ተጨማሪ የልማት ስራዎችን ለማከናወን ይሰራል ብለዋል። የሰላምና የልማት ሥራዎች ለመንግስት ብቻ የሚተው ባለመሆናቸው በየአካባቢው ህብረተሰቡን ያሳተፉ የልማት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ምክትል ከንቲባው አረጋግጠዋል። "ህዝቡ ፍላጎቱ ሰላምና ልማት እንደሆነ በሰላማዊ ሰልፍ ደጋግሞ ጠይቋል" ያሉት አቶ ጌትነት፣ በጫካ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ሀይሎችም የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው እንዲመጡ ህዝቡ የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል። የሰቆጣ ከተማ ነዋሪዎች ባለፈው እሁድ ሰላምና ልማትን የሚደግፍ እና ጽንፈኝነትን የሚያወግዝ ህዝባዊ ሰልፍ ማካሄዳቸው የሚታወስ ነው።
ማህበራዊ
የህዝበ-ሙስሊሙ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ መዋቅራዊ ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን እየተደረገ ነው
Jul 3, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦የህዝበ-ሙስሊሙ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ መዋቅራዊ ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። የመረዳዳት ሥርዓቱን የተሳለጠ ለማድረግ የዘካ እና የአውቃፍ ኮሚሽን ዛሬ በይፋ ተመስርቷል፡፡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኮሚሽኑን ምስረታ በተመለከተ የውይይት መድረክ አካሒዷል፡፡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ተወካይ ሸህ ኢድሪስ አሊ፤ ዘካ ሰዎች ካላቸው በፐርሰንት ተቀንሶ አቅም ለሌላቸው የሚሰጥበት አግባብ ነው ብለዋል፡፡ አውቃፍ ሰዎች በገዛ ፈቃዳቸው ለማህበረሰብ አገልግሎት ለሚውሉ ጉዳዮች ስጦታ እንዲሰጡ የሚያደርግበት መሆኑንም አንስተዋል፡፡ ይህ የዘካና የአውቃፍ ስርዓት ከጥንት ጀምሮ የነበረ ቢሆንም ጊዜያዊ ችግርን ከማስታገስ ውጭ ዘላቂ ሃብትን በመፍጠር ረገድ ጉልህ ሚና እንዳልነበረው ተናግረዋል። የኮሚሽኑ መመስረት ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት የሚያደርጓቸው ድጋፎች ህግ እና ስርዓት ተበጅቶላቸው ፤ዘመናዊ አሰራርን ተከትሎ ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ በማድረግ ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ ለአገራዊ ልማት ትልቅ አቅም እንደሚሆንም እንዲሁ፡፡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የኡለማዎች ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ ጄይላን ኸድር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዘካ እና አውቃፍ የእስልምና እምነት ምሰሶዎች ናቸው ብለዋል፡፡ የኮሚሽኑ መቋቋም የህዝበ-ሙስሊሙን የዘመናት ጥያቄ የሚመልስ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተበታተነ መንገድ ሲደረግ የነበረው የዘካ እና የአውቃፍ የአሰራር ስርዓት ዘመናዊ እንዲሆን ያደርጋልም ነው ያሉት። በዘካና አውቃፍ ኮሚሽን ምሥረታው ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኘተዋል፡፡
ሰብአዊነትን በማስቀደም ሰላምና አብሮነትን በሚያጠናክሩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላይ መሳተፍ የህሊና እርካታ የሚሰጥ ነው - ወጣቶች
Jul 3, 2025 118
ሠመራ፣ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ) ፡- ሰብአዊነትን በማስቀደም ሰላምና አብሮነትን በሚያጠናክሩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላይ መሳተፍ ትልቅ የህሊና እርካታ የሚሰጥ መሆኑን ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣቶች ገለጹ። "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሐሳብ የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣቶች በአፋር ክልል ሠመራ ከተማ የተለያዩ ተግባራት ማከናወናቸውን እንደቀጠሉ ነው። በዛሬው ዕለትም የአፋር ክልል የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለሀገር ሰላም ፣ልማትና እድገት ያለው ሚና ላይ ያተኮረ ልምድ ለወጣቶቹ አካፍለዋል። በዚህ ወቅት ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣቶች እንዳሉት፤ ለሀገርና ለሕዝበ መስራት በጊዜና በቦታ የማይወሰን፤ ትልቅ የህሊና እርካታ የሚሰጥ ተግባር ነው። ከኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣት አህመድ ዓሊ በሰጠው አስተያየት ፤ ኢትዮጵያውያን ከጥንት ጀምሮ የመተጋገዝና የመረዳዳት የዳበረ ባህል ያለን ሕዝቦች ነን ብሏል። በተለይም ሰብአዊነትን በማስቀደም ሰላምና አብሮነትን በሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ መሳተፍ ትልቅ ጥቅም እንዳለው በተግባር ማየቱን ተናግሯል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከማንም በላይ ተሳታፊውን ሰው የሚጠቅም መሆኑን በመረዳት በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ግዴታውን እየተወጣ መሆኑ እንደሚያኮራው ገልጿል። ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን የመጣው ወጣት አቡሽ ንጋቱ በበኩሉ፤ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ሰላምና አብሮነትን በሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑን እና በዚህም የህሊና እርካታ እንደሚሰጠው ተናግሯል። ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ከፍ በሚያደርጉ ተግባራት ላይ በታማኝነት ማገልገል እድለኝነት ነው፤ ከቀደሙ አባቶች መልካምነትን እና ትብብርን መውረስ ያስፈልጋል ብሏል። የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የዜግነት ግዴታ በመሆኑ በወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በመሳተፏ ትልቅ የህሊና እርካታ እንደሰጣትና በዚህም ደስተኛ መሆኗን የተናገረችው ደግሞ ከጋምቤላ ክልል የመጣችው ወጣት ሮዛ ጳውሎስ ናት። ከሐረሪ ክልል የመጣው በጎ ፈቃደኛ ወጣት ሳሊህ እስክንድር፣ ሰብአዊነትን በማስቀደም ለሀገር ልማትና እድገት መስራት የሚያስደስት ተግባር መሆኑን ገለጿል። ዛሬ በኃይማኖት አባቶችና በሀገር ሽማግሌዎች የተሰጣቸው ምክርና የተካፈሉት ልምድ ይበልጥ የሚያበረታታቸው መሆኑን ገልጾ፤ ሰላምና ሕብረ ብሔራዊ አንድነታችንን እንድናጠናክር የሚረዳም ነው ብሏል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሰብአዊ ድጋፍ ጥያቄዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን 268 ሚሊዮን ብር የመጠባበቂያ ፈንድ መቆጠብ ተችሏል
Jul 3, 2025 58
ወላይታ ሶዶ፣ ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ ጥያቄዎችን በራስ አቅም ለመመለስ በተሰራው ሥራ 268 ሚሊዮን ብር የመጠባበቂያ ፈንድ ለመቆጠብ መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ''ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነትና ለተሟላ ክብር'' በሚል መሪ ሃሳብ ሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተጀመረውን ሥራ ለማጠናከር ያለመ የአቅም ግንባታ ስልጠና በወላይታ ሶዶ ከተማ ተሰጥቷል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) እንደገለጹት በክልሉ የሰብዓዊ ድጋፍ ጥያቄዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን በተሰራው ሥራ 268 ሚሊዮን ብር የመጠባበቂያ ፈንድ ማስቀመጥ ተችሏል። አምና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት ''ከተረጂነት ወደ ምርታማነት'' በሚል የተጀመረው ኢኒሼቲቭ በክልሉ ውጤት እያሳየ መሆኑንም አስረድተዋል። ትርፍ በማምረት ለቤተሰብ ፍጆታና ለገበያ ከማቅረብ በተጨማሪ የተለያዩ አደጋዎችን ተከትሎ ለሚነሱ የሰብአዊ ድጋፍ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ስራ መጀመሩንም ገልጸዋል። ለአብነትም ባለፈው የመኸር ወቅት በክልሉ በ1 ሺህ 900 ሄክታር መሬት ለምቶ ከተገኘው ምርት ውስጥ 25 ሺህ ኩንታል የበቆሎ ምርትን ለዚሁ ዓላማ መዋሉን ተናግረዋል። ዘንድሮም የእህል ክምችቱን ለማሳደግ ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው፣ በክልሉ በ6 የክላስተር ማዕከላትና ዞኖች ላይ የእህል መጋዘን መዘጋጀቱን ገልጸዋል። አመራሩ በተፈጠረው ተግባቦት መሠረት ለሥራው ውጤታማነት በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል። በክልሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳ እንደሀገር ከውጭ የሚገባውን ስንዴ በሀገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን የተጀመረው ሥራ ከተረጂነት ለመውጣት እያገዘ ይገኛል ብለዋል። "በዚህ ልክ ከሰራን በአደጋ ጊዜ የሚያስፈልጉ ሰብዓዊ ድጋፎችን በራስ አቅም ማሟላት እንችላለን" ያሉት አቶ ንጋቱ፣ ያለን አቅም አቀናጀቶ በጋራ የመስራቱ ጅምር መጠናከር እንዳለበት ተናግረዋል። በክልሉ ግብርና ቢሮ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጋንታ ጋምአ በበኩላቸው፣ ህዝቡን ከተረጂነት ለማውጣት ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቁመዋል። ሰዎች ሰርተው የሚለወጡበትን አቅም በማሳደግ ከእርዳታ ጠባቂነት ለመውጣት የሚሰሩ ሥራዎች በቀጣይም ሊጠናከሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የጬንቻ ከተማ አስተዳደር ተወካይ አቶ ጬንቻ ጼራ ህብረተሰቡን ከተረጂነት ለማውጣት በአካባቢው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የጊዶሌ ከተማ ከንቲባ አቶ ወልደመድህን ካጫኖ በበኩላቸው ከስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት እና የአካባቢያቸውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ከተረጂነት ለመውጣት እንደሚሰራ ተናግረዋል። ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
በተገነቡልን ተቋሟት የንጹህ መጠጥ ውሀ ችግራችን ተፈቷል-የበደኖ ወረዳ ነዋሪዎች
Jul 3, 2025 57
በደኖ፤ ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ)፦ በተገነቡልን ተቋማት የንጹህ መጠጥ ውሀ ችግራችን ተፈቷል ሲሉ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን በበደኖ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። በወረዳው ከተማና ገጠር ቀበሌዎች ከ92 ማሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ ሁለት የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማቱንም የጨፌ ኦሮሚያ ምክትል አፈ ጉባዔ ኤልያስ ኡመታ እና የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ሚስኪ መሀመድ መርቀዋል። በበደኖ ወረዳ ኦዳ ቢሻን ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነዋሪ ወይዘሮ ማሾ መሀመድ በሰጡት አስተያየት፤ ቀደም ሲል በአካባቢው የውሃ ተቋም ባለመኖሩ ከርቀት አካባቢ በመቅዳት ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ያጠፉ እንደነበር ተናግረዋል። አሁን ላይ በአካባቢያቸው የተገነባው የውሃ ተቋም ለአገልግሎት በመብቃቱ ችግራቸው መፈታቱን ገልጸዋል። የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋሙ ከውሀ ወለድ በሽታዎች እንደሚታደጋቸውም ተናግረዋል። ሌላው የቀበሌው ነዋሪ አቶ አብደላ አባስ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል የውሃ ተቋም ባለመኖሩ ለመጠጥና ለከብቶች የሚሆን ውሃ ለማግኘት ረጅም ርቀት ይጓዙ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህም በግብርና ስራቸው ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ማሳደሩን ጠቁመው አሁን ላይ መንግስት የገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ የቆየ ጥያቄያቸውን መመለሱን ገልፀዋል። የበደኖ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ራዚያ አብዱላሂ በበኩላቸው በከተማው ተገንብቶ በየቀበሌው የተዳረሰው የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግሩን መቅረፉን አመልክተዋል። የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ውሃና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጀማል ሀሰን፤ በበጀት ዓመቱ በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች በ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወጪ 55 አዳዲስ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት በቅተዋል። በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች በተከናወነው የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ 90 ሺህ የሚደርሱ ነዋሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ሚስኪ መሀመድ በበኩላቸው የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች የመመለስ ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። መሰረተ ልማቶችን በፍጥነትና በጥራት ገንብቶ ለአገልግሎት የማብቃት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ኢኮኖሚ
በሕገወጥ የነዳጅ ግብይት በተሰማሩ 562 ነዳጅ ማዳያዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል
Jul 3, 2025 89
አዲስ አበባ፤ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በሕገወጥ የነዳጅ ግብይት በመሰማራት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ችግር በፈጠሩ 562 የነዳጅ ማደያዎች ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ የነዳጅ ማዳያዎች፣ የነዳጅ አጓጓዦች እና ኩባንያዎች ጋር በዘርፉ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂዷል። በዚሁ ወቅት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) እንዳሉት በሕገወጥ መንገድ ሰውሰራሸ የነዳጅ እጥረት በመፍጠር ችግር እየፈጠሩ ባሉ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል። በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚገባው ነዳጅ ለዜጎች የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴና ለኢኮኖሚ ወሳኝ የመሆኑን ያህል ያለአግባብ ለመክበር በነዳጅ ላይ ሰው ሰራሽ የዋጋ ንረት የሚፈጥሩ አካላት መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ሚኒስቴሩ ባደረገው ክትትል በሕገወጥ የነዳጅ ግብይት ተሰማርተው ባገኛቸው 562 ነዳጅ ማዳያዎች ላይ የተለያየ ደረጃ ያለው አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን ጠቁመዋል። ከ222 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ቅጣት እንደተጣለባቸው ጠቅሰው፣ 54 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ሥር ውለው መጠየቃቸውንና በሕገወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ መወረሱንም አንስተዋል። በቀጣይ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የነዳጅ ስርጭት በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚተገበር ገልጸው፥ ሕግን አክብረው በመስራት የሀገር ባለውለታ የሆኑ ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል። በዚህም በሀገሪቱ ነዳጅ እያቀረቡ ባሉት 60 የነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የሚደረገው ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለፅ፥ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት የጋራ ስራዎች ይተገበራሉ ነው ያሉት። የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅ በበኩላቸው፥ በመዲናዋ የነዳጅ አቅርቦት ላይ በየቀኑ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በአግባቡ ሕዝቡን በማያገለግሉ አካላት እና ግብይቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማይፈጽሙት ላይ እየተወሰደ ያለው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በውይይቱ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች በበኩላቸው በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ቅንጅታዊ ሥራ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) በሰጡት ምላሽ፥ መንግሥት የነዳጅ ሪፎርም ካደረገ በኋላ በርካታ መሻሻሎች መኖራቸውን ገልጸዋል። ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የነዳጅ አቅርቦት በ10 በመቶ መጨመሩን ጠቅሰው፥ ከአቅርቦት ጋር የተያያዘ ችግር አለመኖሩን ጠቅሰዋል። ነዳጅ ማጓጓዝን በተመለከተ በቀጣይ በተሻለ ሁኔታ በባቡር በብዛት የማጓጓዝ፣ የመሰረተ ልማት ሁኔታዎችን የማሻሻል እና የዘርፉ ተዋናዮች የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች በዘላቂነት የመፍታት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ የጀመረው በረራ የኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር ያግዛል
Jul 3, 2025 63
አዲስ አበባ፤ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ የጀመረው በረራ ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተገለጸ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአገልግሎት ዘርፉ ከተመዘገቡ እድገቶች እና ውጤቶች መካከል አንዱ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሣምንት አራት ጊዜ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ ከተማ አዲስ በረራ ትናንት በይፋ አስጀምሯል። አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ ያደረገውን የመጀመሪያ የመንገደኞች በረራ አስመልክቶም ዛሬ በፖርቶ ከተማ የባለድርሻ አካላት የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የፓናል ውይይቱ በዋናነት የአየር መንገዱ የሚያደርገውን በረራ በኢኮኖሚያዊ ትስስር ይበልጥ ማጠናከር ላይ ያለመ ነው። በፓናል ውይይቱ ከተሳተፉት መካከል የፖርቶ አውሮፕላን ማረፊያ ዋና ዳይሬክተር ሩይ አልቬዝ፤ አየር መንገዱ የጀመረው በረራ ሁለቱ አገራትን በተለያዩ መስኮች ለማስተሳሰር እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የዛሬው የፓናል ውይይትም በረራውን በካርጎ አገልግሎት ለማስተሳሰር ያላቸውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ በውይይቱ በካርጎ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶችና ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውን ጠቅሰዋል። በፖርቶ አየር መንገድ ዋና የንግድ ኦፊሰር የሆኑት ካረን ስትራውጎ በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ የጀመረው በረራ አፍሪካን ብቻ ሳይሆን በስፔን በኩል አድርገን ከአውሮፓ ጋር ለመተሳሰር ያግዘናል ብለዋል። ፖርቶ የኢንዱስትሪ ከተማ መሆኗን አንስተው፤ ከዚህ አኳያ አየር መንገዱ የጀመረው በረራ ከኢኮኖሚ ትስስር አንጻር ትርጉም ያለው ለውጥ እንደሚያመጣ ያላቸውን እምነት ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፍጥነት እያደገ ያለ ስመጥር አየር መንገድ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የአውሮፕላን ቴክኖሎጂ ባለሙያ የሆኑት ጆን ጆርጅ ናቸው። የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለረዥም ጊዜ እንደሚያውቁት የሚናገሩት ጆን ጆርጅ፤ የአየር መንገዱ የፖርቶ በረራም ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በፖርቹጋል የሚኖሩ ዜጎች ወደ ተለያዩ ሀገራት በቀላሉ እንዲጓዙ እንደሚያስችል ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ በአገልግሎት ዘርፉ ከተመዘገቡ እድገቶች እና ውጤቶች መካከል አንዱ ማሳያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሆኑን አንስተዋል። አየር መንገዱ በተያዘው ዓመት ተጨማሪ 13 አውሮፕላኖችን በመግዛት አጠቃላይ የአውሮፕላን ብዛቱ 180 መድረሱን በመጠቆም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፤ ስድስት ተጨማሪ አዳዲስ መዳረሻዎችን በመጨመር አጠቃላይ ያላውን የመዳረሻ ብዛት ወደ 136 አሳድጓል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2035 ዓመታዊ ገቢውን ወደ 25 ቢሊየን ዶላር ከፍ ለማድረግና በዓመት 67 ሚሊዬን መንገደኞችን ለማጓጓዝ ራዕይ አስቀምጦ እየሰራ ይገኛል።
በክልሉ ለድህነት ቅነሳ ተግባራትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት ይሰጣል-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Jul 3, 2025 97
ሀዋሳ፤ ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል በድህነት ቅነሳ ተግባራት ላይ በማተኮር ገበያን ማረጋጋትና የሥራ ዕድል መፍጠር ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡ ክልሉ የተመሰረተበትን 5ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ክልሉ በአዲስ መልክ ከተደራጀ በኋላ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በዚህም የተመዘገቡ ስኬቶች እንዳሉ ገልጸው፣ የስኬቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ተሞክሮዎችን ማስፋት፣ ማነቆዎችን መፍታትና በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በቀጣይም ድህነትን በሚቀንሱ ተግባራት ላይ በማተኮር ገበያን ማረጋጋት፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠርና የቤተሰብ ብልጽግናን ማረጋገጥ የክልሉ መንግስት ትኩረቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። ለዚህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአቅርቦት እጥረት ችግርን በመፍታት የእያንዳንዱን ቤተሰብ ህይወት ለመቀየር የተቀረጸውን ፓኬጅ በመተግበር የህብረተሰቡን ገቢ ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል፡፡ በክልሉ ለወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር የተገኙ ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳደድሩ፣ በቀጣይ ተጨማሪ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ቀድመው ወደሥራ የገቡትን የመደገፍ ሥራ ይሰራል ብለዋል፡፡ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የተጀመሩ ሥራዎች እያስገኙ ያሉትን ውጤት በማስቀጠል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የህዝብን እርካታ ማረጋገጥ ሌላው ትኩረት መሆኑንም ጠቅሰዋል። በውይይት መድረኩ ከክልሉ መንግስት ዕቅድ ጋር የሚጣጣሙ ሀሳቦች መንጸባረቃቸውን ገልጸው፣ የክልሉን እድገት ለማፋጠን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። የክልሉን የአምስት ዓመታት ጉዞ ሰነድ ለውይይት ያቀረቡት የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በበኩላቸው በመሰረተ ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ሥራዎች ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ የሰጡ ናቸው ብለዋል። በዚህም ባለፉት አምስት ዓመታት ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ከ1 ሺህ 400 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። የክልሉን የመጠጥ ውሃ ሽፋኑን ወደ 64 በመቶ ያሳደጉ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውንም ተናግረዋል፡፡ በትምህርት ዘርፍም ቅድመ መደበኛ ላይ ትኩረት በማድረግ ባለሃብቱንና ህዝቡን በማስተባበር የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ መከናወኑን ገልጸው፣ በዚህም ከፍተኛ ለውጥ መታየቱንም ጠቁመዋል፡፡ አራርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት በግብርና፣ በእንስሳትና ዓሣ ሃብት ልማት ምርታማነትና ገቢን ለማሳደግ የተሰሩ ሥራዎችም በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ድርሻ አላቸው፡፡ የሲዳማ ክልል ከተደራጀ በኋላ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎችና በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ትናንት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተጎብኝተዋል። በዛሬው መድረክም በመስክ ምልከታ በታዩ ጉዳዮችና በቀረበው ሰነድ ላይ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በጋራ መክረዋል።
የዘንድሮው በጀት ዓመት በኢትዮጵያ ታሪክ ታይተው የማይታወቁ ድሎች የተመዘገቡበት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jul 3, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የዘንድሮው በጀት ዓመት በኢትዮጵያ ታሪክ ታይተው የማይታወቁ ድሎች የተመዘገቡበት የማንሰራራት ዓመት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የማክሮ ኢኮኖሚ ስብራት፣ የግሉ ዘርፍ እንዲነቃቃ ምቹ ሁኔታ አለመኖር፣ የምርታማነት ውስንነት መኖርና በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ የሆነ ኢኮኖሚ አለመኖር ለማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም መነሻ መሆናቸውን አንስተዋል። ሪፎርሙ ከውጭ ባለን ትስስር ልናገኝና ልናጣ የምንችለውን በሀገር አቅም ልናገኝ የምንችለውን በለካ መንገድ የተቀመጠ ነውም ብለዋል። በኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የ8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ተመዝግቦ እንደነበር በማውሳት፥ በዚህ ዓመት አጠቃላይ 8 ነጥብ 4 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት ታቅዶ ሲሰራ ቆይቷል ነው ያሉት። ላለፉት ዓመታት 27 ሚሊየን በሴፍቲኔት የታቀፉ ተረጂዎች እንደነበሩ አንስተው፤ በግብርናው ዘርፍ በተሰራው ስራ ዘንድሮ 23 ሚሊዮን ዜጎችን ከሴፍቲኔት ተጠቃሚነት በራሳቸው አቅም ወደ መተዳደር መሸጋገራቸውን ተናግረዋል። ይህ የማንሰራራት ትልቅ ማሳያ መሆኑን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በቀጣይም ቀሪዎቹን ከተረጂነት በማላቀቅ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ብርቱ ስራ ይጠይቃል ብለዋል። የዘንድሮው በጀት ዓመት የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞ የተጀመረበትና በሀገሪቱ ታሪክ ታይተው የማይታወቁ ድሎች የተመዘገቡበት መሆኑን አመላክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም በበጀት ዓመቱ 900 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረው፥ የዋጋ ግሽበትን አምና ከነበረበት 22 ነጥብ 8 በመቶ ወደ 14 ነጥብ 4 በመቶ ማውረድ መቻሉንም ገልጸዋል። ከወጭ ንግድ ከ8 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ጠቅሰው፤ የአገልግሎት ዘርፍ፣ ሬሚታንስ እና ሌሎች የውጭ ምንዛሪ ማግኛ ምንጮችን ጨምሮ በድምሩ 32 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ከ150 በላይ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶች ማስተናገዷን ገልጸው፥ ይህም ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር በእጥፍ መጨመሩን አንስተዋል። በዚህ ዓመት ብቻ የአንድነት ፓርክ፣ ሳይንስ ሙዚየም፣ የወዳጅነት ፓርክና ቤተ መንግስትን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሰዎች የጎበኙ ሲሆን ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ብለዋል። በዓመት 600ሺህ ቶን መስታወት የማምረት አቅም ያለው ፋብሪካ እየተገነባ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ፋብሪካው ዘመናዊ የኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚፈልገውን የመስታወት ምርት በጥራት ለማቅረብ የሚችል መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በቂ የመስታወት ፋብሪካ አልነበራትም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አሁን የሀገር ውስጥ ጥሬ እቃ ሙሉ ለሙሉ የሚጠቀም ፋብሪካ መገንባት መጀመሯን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው በአዲሱ ዓመት መጀመሪያ ኢትዮጵያ የጋዝ ምርቷን ወደ ውጭ ገበያ ማቅረብ እንደምትጀምርና የማዳበሪያ ፋብሪካ እንደምትገነባም ይፋ አድርገዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የመጤ የአረም ዛፍ (ፕሮሶፒስ) ወደ ባዮማስ ኃይልነት በመቀየር የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመቀነስ እየተሰራ ነው
Jul 3, 2025 90
ድሬዳዋ፣ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ) ፦የመጤ የአረም ዛፍን (ፕሮሶፒስ) ወደ ባዮማስ ኃይልነት በመቀየር የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመቀነስና የስራ ዕድል ለመፍጠር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከፕሮሶፒስ ዛፍ የባዮማስ ኃይልን የማምረት የሙከራ ፕሮጀክት እንዲሳካ ግንባር ቀደም ተሳትፎ ላደረጉ ግለሰቦችና ተቋማት በድሬዳዋ ዕውቅናና ሽልማት አበርክቷል። በኢትዮጵያ በጠቅላላው በ2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ተንሰራፍቶ የሚገኘው 'ፕሮሶፒስ' የተሰኘው መጤ አረም በአፋርና በሶማሌ ክልሎች የግጦሽና የእርሻ መሬትን በመውረር ጉዳት እያደረሰ ይገኛል። ይህንን መጤ አረም በማጨድና በመፍጨት ለኃይል አማራጭነት በማዋል ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች እንደ ድንጋይ ከሰል በመሆን አገልግሎት እንዲሰጥ ጥናት ሲደረግ ቆይቶ ወደ ተግባር መገባቱ ይታወቃል። በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የአየር ንብረት ለውጥ ስራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት አለሙ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ለሲሚንቶ ምርት ኃይል አቅርቦት የድንጋይ ከሰልን ከውጭ ለማስገባት በየዓመቱ እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ታደርጋለች። "ይህን ወጪ ለመቀነስ የ'ፕሮሶፒስ' ዛፍን ወደ ባዮማስ ኃይልነት ለመቀየር የተጀመረው የሙከራ ፕሮጀክት ኃይልን በማምረት ከፍተኛ አቅምን ሊፈጥር ስለሚችል ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲሸጋገር በቅንጅት እየተሰራ ነው" ብለዋል። ለዚህ የሙከራ ስራ መሳካት ናሽናል ሲሚንቶ ያበረከተው አስተዋጽኦ በአርዓያነት የሚጠቀስ መሆኑን አንስተዋል። ለሲሚንቶ ምርት ከውጭ የሚገባን የድንጋይ ከሰልን ምርት መጠን ለመቀነስ መጤ አረሙን ወደ ባዮማስ ኃይልነት በመቀየር የውጭ ምንዛሬን ለመቀነስ እና ለአርብቶ አደሩ የስራ ዕድል ለመፍጠር መሰራቱን አክለዋል። ሽልማቱ ከተበረከተላቸው መካከል የኢስት አፍሪካ ሆልዲንግ መስራችና ባለቤት አቶ ብዙአየሁ ታደለ በኢትዮጵያ ለሲሚንቶ ማምረቻ በውጭ ምንዛሬ የምታስገባውን የድንጋይ ከሰል ለመተካት የሚያስችል ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። ፕሮሶፒስን ወደ ባዮማስ ኃይል ለመለወጥ ላከናወኑት የሙከራ ፕሮጀክት ዕውቅና እንደተሰጣቸው ገልፀው ወደ ባዮማስ ኃይልነት ለመለወጥም በግብፅ፣ በአውሮፓና በላቲን አሜሪካ በመዘዋወር ልምድ መቅሰማቸውን ገልጸዋል። ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት ፕሮጀክቱን ወደ ስራ በማስገባት በናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የተደረገው የሙከራ ፕሮጀክት ስራ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም የድንጋይ ከሰልን በባዮማስ በመተካት በለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል። ሌሎች የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የባዮማስ ኃይልን እንዲጠቀሙ ልምዳቸውን ለማካፈልና ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
በክረምት ወራት የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በመውሰድ የቴክኖሎጂ አቅም እና ተወዳዳሪነታችንን ለማሳደግ እንሰራለን- ተማሪዎች
Jul 3, 2025 98
ዲላ፤ ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ)፦በክረምት ወራት ተጨማሪ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በመውሰድ የቴክኖሎጂ አቅምና ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ እንደሚሰሩ በጌዴኦ ዞን የሚገኙ ተማሪዎች ገለጹ። በዞኑ በክረምት ወራት ከ3 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅት መደረጉም ተመላክቷል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ተማሪዎች መካከል የዲላ ዶንቦስኮ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ቅድስት ወርቅአየሁ ቀደም ሲል በፕሮግራም ፋንዳሜንታል ዘርፍ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስዳ የምስክር ወረቀት ማግኘቷን ገልጻለች። ይህም በሶፍት ዌር ግንባታ አቅም እንደፈጠረላት ገልጻ በክረምት ወራትም በሌሎች የኢትዮ ኮደርስ ዲጂታል ስልጠና ዘርፎች የሚሰጠውን ስልጠና በመከታተል ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ መዘጋጀቷን ገልጻለች። በሕጻናት ጌምና ጨዋታ በአፍሪካ ኮደረስ ቻሌንጅ ውድድር የፈጠራ ሥራዋን በማቅረብ ተሸላሚ መሆኗን ያነሳችው ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ተማሪ ከነአን አንትንብዬ ናት። ከዚህ ቀደም የወሰደችው የኮደርስ ስልጠና የፈጠራ አቅሟን እንዳሳደገላት ጠቁማ፣ በክረምት ወራት ስልጠናውን በማጠናከር ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ መዘጋጀቷን ተናግራለች። በዲላ ከተማ የሚገኘው ቆፌ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ቤዛኩሉ ገዛኸኝ በበኩሉ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በቀለም ትምህርት ያለውን ውስን እውቀት በማስፋት ተግባራዊ እውቀት እንዲጨብጥ ያደረገው መሆኑን ተናግሯል። ስልጠናው ለቴክኖሎጂ ያለውን ቅርበት እንዳሳደገለት ገልጾ፣ በዲጂታል ዓለም ብቁ ሆኖ ለመገኘትና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የስልጠናው ፋይዳ የጎላ መሆኑን ተናግሯል። የክረምት ወራት የእረፍት ጊዜውን በኢትዮ ኮደርስ ተጨማሪ ስልጠና በመውሰድ አቅሙን ለማሳደግ ማቀዱንም ገልጿል። በትምህርት ቤቱ ከ150 በላይ ተማሪዎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ የዲላ ዶንቦስኮ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር አንዱአለም ፀጋዬ ናቸው። ስልጠናውን የወሰዱ ተማሪዎች የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ የአስተሳሰብ አድማሳቸውን እንዲያሰፉ ከማድረግ ባለፈ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራዎችን የማበልጸግ ሥራ መጀመራቸውን ተናግረዋል። በተያዘው ክረምት ወራትም በትምህርት ቤቱ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን አጠናክሮ ለማስቀጠል ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል። የጌዴኦ ዞን ሳይንስ፣ ኢንፎርሜንሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ ሃላፊ አቶ ደረጀ ሾንጣ በበኩላቸው እንዳሉት በክረምት ወራት በዞኑ ከ3 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል። ለዚህም በከፍተኛ እና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የስልጠና ማዕከላትን የማጠናከርና የኔትወርክ ዝርጋታ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ በዞኑ 9 ሺህ 714 ዜጎችን በኢትዮ ኮደርስ ለማሰልጠን ታቅዶ ወደስራ መገባቱንም አቶ ደረጀ አስታውሰዋል። እስካሁንም ስልጠናውን ለመውሰድ ከ8ሺህ በላይ ዜጎች እንደተመዘገቡ ጠቁመው፣ ከእነዚህ ውስጥ 3ሺህ 400 ዎቹ ስልጠናቸውን አጠናቀው የምስክር ወረቀት አግኝተዋል ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም ስልጠናውን እየተከታተሉ ያሉ ዜጎች አሉ ያሉት አቶ ደረጀ፣ በክረምትም ስልጠናውን አጠናክሮ በማስቀጠል ከዕቅድ በላይ ለማስመዝገብ እንደሚሰራ ተናግረዋል። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የዜጎችን የቴክኖሎጂ እውቀት በማጎልበት የፈጠራ አቅማቸውንና ተወዳዳሪነታቸውን እያሳደገው መሆኑን ጠቅሰው፣ የስልጠናው ተሳታፊዎችም ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jul 3, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሙስናን በተመለከተ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን ብለዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስታዊ ሙስና የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገር ግን ከአገልግሎት አንጻር ትናንሽ የሙስና ተግባራት አሉ ብለዋል። ይህን ለማስተካከል ወደ ስራ የገባው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሶስት ወራት ብቻ 23 ተቋማትን በማካተት 124 አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። አሁን አንድ ማዕከል ብቻ ነው ያለው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን መሶብ እየተስፋፋ አገልግሎት እየዘመነ ሲሄድ የእጅ በእጅ ሙስና እየቀነሰ ይሄዳል ሲሉም አስታውቀዋል። ከዚያ ውጭ ሙስናን መፀየፍ የግለሰቦችን አመለካከትና ውሳኔን የሚጠይቅ መሆኑንም ማወቅ ይገባል ነው ያሉት። ሙስናን የምንከላከለው በስርዓት ነው፤ በዘረጋነው የመሶብ ስርዓትም ተገልጋዮች ከ90 በመቶ በላይ እርካታ አሳይተዋል ይህንን በሁሉም አካባቢዎች ማስፋት ከተቻለ ሙስና በእጅጉ ይቀንሳል ብለዋል በማብራሪያቸው።
40 የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀት አገኙ
Jul 2, 2025 156
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ በአቪዬሽን ሴኪዩሪቲ ጥራት ቁጥጥርና አደጋ አስተዳደር የሰለጠኑ 40 የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳመለከተው፤ በኢትዮጵያ አጠቃላይ የአቪዬሽን ሴኪዩሪቲ ስራዎችን በበላይነት ለመምራት በአዋጅ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋሙ ከዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ጋር በመተባበር በአቪዬሽን ሴኪዩሪቲ ጥራት ቁጥጥርና በአቪዬሽን አደጋ አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና የወሰዱ 40 ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ ማድረጉን ገልጿል። የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ከ12 ዓመታት በኋላ በኢትዮጵያ የአቪዬሽን ሴኪዩሪቲ አሰራሮች ላይ ባደረገው ኦዲት ሀገራችን ምንም ዓይነት የሴኪዩሪቲ ስጋት እንደሌለባት ማረጋገጡን አስታውሷል። ይህን ተከትሎም ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የሲቪል አቪዬሽን ደኅንነት ዋና መምሪያ ጋር በተፈጠረው መልካም ግንኙነትና ትብብር ስልጠናው ከዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት በመጡ ባለሙያዎች ከሰኔ 9 እስከ ሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሰጥቷል። ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀቱ አየር መንገዱ ተደራሽ በሚሆንባቸው ሀገራት ሁሉ የአቪዬሽን ሴኪዩሪቲ የጥራት ቁጥጥር ተግባራትን ለማካሄድ የሚያስችል መሆኑን የገለጹት ከዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት የመጡት አሰልጣኞች፤ ባለሙያቹ ስልጠናውን በስኬት ማጠናቀቃቸውን ጠቁመዋል። ስልጣኞች ያገኙት ዕውቀት ተቋሙ ሀገራዊ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት ለመፈፀም የሚያስችለው ከመሆኑም ባለፈ፤ ኢትዮጵያን ለአቪዬሽን ደህንነት ዘርፍ እየሰጠች ያለችው ልዩ ትኩረት ጉልህ ማሳያ ተደርጎም ሊወሰድ እንደሚችል የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አመልክቷል። የአቪዬሽን ደህንነት ጠንካራ የጥራት ቁጥጥር ትግበራ እና የአደጋ ምላሽ አሰጣጥ ዝግጁነት የእያንዳንዱ የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት አባል ሀገራት ኃላፊነት መሆኑን ያስታወቀው አገልግሎቱ ፤ ይህም የአቪዬሽን ኢንዱስትሪውን ደኅንነት በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ መሰረት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጿል፡፡ በስልጠናው የተገኘውን ዕውቀት፣ ክህሎት እና የአስተሳሰብ ለውጥ በቀጣይ በአቪዬሽን ደህንነት ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን ለተያዘው ራዕይ እና አጠቃላይ ተቋማዊ ስትራቴጂ ግብዓት አድርጎ በማዋል የኢትዮጵያ አየር መንገድን ተመራጭነት ይበልጥ በማሳደግ ሀገራዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ስፖርት
የአየር ኃይል ሶስተኛ አየር ምድብ የስፖርት ውድድር ተጠናቀቀ
Jul 2, 2025 116
ድሬዳዋ፣ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦በኢፌዴሪ አየር ኃይል ሶስተኛ አየር ምድብ ለሁለት ሳምንት ሲካሄድ የሰነበተው የስፖርት ውድድር ማምሻውን ተጠናቀቀ። በምድቡ ከሰኔ 11 ቀን 2017 ጀምሮ በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ሲካሄድ የሰነበተው ውድድር ዛሬ ማምሻውን በተደረገ የእግር ኳስ ጨዋታ ተጠናቋል ። በወንዶች በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ የሶስተኛ አየር ምድብና የሆርሞድ ጤና ቡድን መደበኛውን የጨዋታ ጊዜ ያለምንም ጎል ተለያይተዋል። አሸናፊውን ለመለየት በተሰጡ የፍፁም ቅጣት ምቶች ሆሮሞድ አራት ለአንድ በሆነ ውጤት አሸናፊ ሆኗል። ከወንዶች እግር ኳስ በተጨማሪም በምድቡ የተለያዩ ክፍሎች መካከል የአትሌቲክስ፣ የመረብ ኳስ ፣የእጅ ኳስና ሌሎች ውድድሮች በሁለቱም ፆታ የተካሄዱ ሲሆን ለአሸናፊዎቹ ሽልማት ተበርክቷል። ለአሸናፊዎች የተዘጋጀውን የዋንጫና ሌሎች ሽልማቶች የሰጡት የኢፌድሪ አየር ኃይል ሶስተኛ ምድብ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ደረጀ ቡሽሬ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ናቸው። ዋና አዛዡ ኮሎኔል ደረጀ ቡሽሬ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ ስፖርት የሠራዊቱን አካላዊ ብቃትና ስነ ልቦናዊ ጥንካሬ በማዳበር የትኛውንም ግዳጅ በታላቅ ብቃት እንዲወጣ እያገዘ ይገኛል ። እየተጠናቀቀ በሚገኘው በጀት አመት ምድቡ በተለያዩ ተልዕኮዎቹ ውጤታማ ተግባራት ማከናወኑንም ጠቅሰዋል። በውድድሩ የከተማው አምስት የጤና ቡድኖች መሳተፋቸው ሠራዊቱ ከማህበረሰቡ ጋር ያለውን ሁለንተናዊ ትስስር እንዲጠናከር አጋጣሚ የተፈጠረበት መሆኑን አንስተዋል ። ዛሬ ማምሻውን በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ የከተማው የስፖርት ቤተሰቦች በስፍራው ተገኝተው ውድድሩን ተመልክተዋል።
ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለ
Jul 2, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ የመጨረሻ መርሃ ግብር ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ሞንቴሬይን 2 ለ 1 አሸንፏል። ትናንት ከእኩለ ሌሊት በኋላ በሜርሴዲስ- ቤንዝ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የጊኒው አጥቂ ሴርሁ ጉይራሲ በ14ኛው እና በ24ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥሯል። ሜክሲኳዊው አጥቂ ጀርመን ቤርቴራሜ በ48ኛው ደቂቃ ሞንቴሬይን ከሽንፈት ያልታደገቸውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ተጨማሪ ግቦችን ሊያስቆጥርባቸው የሚችልባቸውን እድሎች አልተጠቀመም። የጊኒው አጥቂ ሴርሁ ጉይራሲ የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለ የመጨረሻው ቡድን ሆኗል። በሩብ ፍጻሜው ከሪያል ማድሪድ ጋር ይገናኛል ። ማድሪድ ትናንት ማምሻውን ጁቬንቱስን 1 ለ 0 አሸንፏል። የጥሎ ማለፍ መርሃ ግብሮች የተጠናቀቁ ሲሆን የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ሰኔ 27 እና 28 ቀን 2017 ዓ.ም ይደረጋሉ። ፓልሜራስ ከቼልሲ፣ ፒኤስጂ ከባየር ሙኒክ፣ ፍሉሜኔንሴ ከአል ሂላል እና ሪያል ማድሪድ ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ በሩብ ፍጻሜው የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው።
ሪያል ማድሪድ ጁቬንቱስ በማሸነፍ ለሩብ ፍጻሜ አልፏል
Jul 2, 2025 101
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ማለፍ ተጠባቂ መርሃ ግብር ሪያል ማድሪድ ጁቬንቱስን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻዉን በሃርድ ሮክ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የ21 ዓመቱ አጥቂ ጎንዛሎ ጋርሺያ በ54ኛው ደቂቃ ከትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ የተሻገረለትን ኳስ በግሩም ሁኔታ በግንባሩ ገጭቶ በማስቆጠር ሎስ ብላንኮሶቹን አሸናፊ አድርጓል። ተስፈኛው ወጣት አጥቂ ጋርሺያ በውድድሩ ያስቆጠራቸውን ግቦች ብዛት ወደ ሶስት ከፍ አድርጓል። ሪያል ማድሪድ በጨዋታው የተሻለ ኳስ ቁጥጥር የነበረው ሲሆን ለግብ የቀረቡ እድሎችንም መፍጠር ችሏል። ጉዳት ላይ የነበረው ኪሊያን ምባፔ ተቀይሮ በመግባት በዓለም ዋንጫው የመጀመሪያ ተሳትፎውን አድርጓል። ጁቬንቱስ በመልሶ ማጥቃት ግብ ለማስቆጠር ወደ ሜዳ ይዞ የገባው የጨዋታ ስልት ውጤታማ አልነበረም። ውጤቱን ተከትሎ ሪያል ማድሪድ የሩብ ፍጻሜ ትኬቱን ቆርጧል። ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ እና ሞንቴሬይ አሸናፊ ጋር ይጫወታል። በጥሎ ማለፉ የመጨረሻ መርሃ ግብር ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ከሞንቴሬይ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በሜርሴዲስ-ቤንዝ ስታዲየም ይጫወታሉ።
የአውሮፓ ስመ ገናናዎቹ ሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱስ ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Jul 1, 2025 133
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሃ ግብር የመጨረሻ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሀርድ ሮክ ስታዲየም ሪያል ማድሪድ ከጁቬንቱስ የሚያደርጉት ጨዋታ የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያን ቀልባቸውን ጥለውበታል። የአምስት ጊዜ የፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ አሸናፊው ሪያል ማድሪድ በምድብ ስምንት በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ በመሆን ማጠናቀቁ ይታወቃል። በውድድሩ የመጀመሪያ ተሳትፎውን እያደረገ የሚገኘው ጁቬንቱስ በምድብ ሰባት ስድስት ነጥብ በማግኘት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብቷል። የአውሮፓ ኃያላኑ ሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱስ በሁሉም ውድድሮች እስከ አሁን 21 ጊዜ ተገናኝተዋል። ሪያል ማድሪድ 10 ጊዜ በማግኘት ውስን ብልጫ ወስዷል። ጁቬንቱስ 9 ጊዜ ሲያሸንፍ 2 ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። በ21ዱ ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ 26 ግቦችን ሲያስቆጥር ጁቬንቱስ 25 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሁለቱ ክለቦች ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት እ.አ.አ በ2017 በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ነበር። በካርዲፍ በተካሄደው ጨዋታው ሪያል ማድሪድ 4 ለ 1 በማሸነፍ ዋንጫውን አንስቷል። በአውሮፓ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ትልቁ የክለቦች ባላንጣነት ማሳያ ተደርጎ የሚጠቀሰው የቡድኖቹ ፍልሚያ ሁሌም ጠንካራ እና እልህ አስጨራሽ ፉክክር የሚደረግበት ነው። ሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱስ የየሊጋቸውን ዋንጫ በተመሳሳይ 36 ጊዜ በማንሳት የበላይነቱን ይዘዋል። በአውሮፓ መድረክ ሪያል ማድሪድ 15 ጊዜ የሻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ ከፍ በማድረግ ስኬታማ መሆን የቻለ ክለብ ነው። ጁቬንቱስ ሁለት ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አንስቷል። የእግር ኳስ ባለሙያዎች ከወቅታዊ ብቃት አንጻር ሪያል ማድሪድ ጁቬንቱስን በጠባብ የግብ ልዩነት ሊያሸንፍ ይችላል የሚል ግምታቸውን አስቀምጠዋል። በጥሎ ማለፍ የመጨረሻ መርሃ ግብር ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ከሞንቴሬይ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በሜርሴዲስ ቤንዝ ስታዲየም ይጫወታሉ። ቦሩሲያ ዶርትሙንድ በሰባት ነጥብ የምድብ ስድስት መሪ፣ ሞንቴሬይ በምድብ አምስት በአምስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዘው ጥሎ ማለፍ ገብተዋል። ሁለቱ ክለቦች እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የሁለቱ ጨዋታ አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው ይገናኛሉ። በአሜሪካ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ፒኤስጂ፣ ባየር ሙኒክ፣ ቼልሲ፣ ፓልሜራስ፣ አል ሂላል እና ፍሉሜኔንሴ እስከ አሁን ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀሉ ክለቦች ናቸው።
አካባቢ ጥበቃ
ተማሪዎች በሀገር ልማት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ሊያጠናክሩ ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ
Jul 3, 2025 126
ጋምቤላ ፤ ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ)፡- ተማሪዎች በሀገር ልማት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ሊያጠናክሩ ይገባል ሲሉ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ በመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድን ጨምሮ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ከጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ጋር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። ርዕሰ መስተዳድሯ አለሚቱ ኡሞድ፣ በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ እንዳሉት ተማሪዎች በሀገሪቱ የልማት ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል። መንግስት የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማቶች ለማሳደግ በሚያደረገው ጥረት የተማሪዎች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑንም ተናግረዋል። ዛሬ በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች ጋር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርም ይህንኑ ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ገልፀዋል። ተፈታኝ ተማሪዎችም በክረምቱ የእረፍት ጊዜያቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላይ በንቃት በመሳተፍ የአካባቢያቸውን ህዝብ ማገልገል እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የጋምቤላ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ድሪባ ኢቲቻ (ዶ/ር) በቡኩላቸው የ2017 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል። ተፈታኝ ተማሪዎቹም ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ማከናወናቸው በሀገር ልማት አሻራቸውን የሚያሳርፉበትን እድል ማስፋቱን ገልፀዋል። ከተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች መካከል ተማሪ ላትጆር ቱትና ተማሪ ኮንግ ጆክ በሰጡት አስተያየት ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ላይ መሳተፋቸው ለሀገራቸው እድገት የበኩላቸውን ሚና የሚያበረክቱበትን አጋጣሚ መፍጠሩን ጠቁመዋል። ዛሬ በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ የጀመሩቱን የአረንጓዴ አሻራ ልማት ወደ መጡበት አካባቢ ሲመለሱም ወጣቶችን በማስተባበር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።
በአማራ ክልል ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል
Jul 2, 2025 124
ባህርዳር ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምህረት፤ ለክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተደረገውን አጠቃላይ ዝግጅት በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም በክልሉ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርጋ ግብር ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ከእነዚህ መካከል 20 ሚሊዮን የሚሆነው የቡና እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውንም ተናግረዋል። ለችግኝ ተከላው ቀደም ብሎ መሬት በመለየት የጉድጓድ ቁፋሮ እና ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች መደረጋቸውን አንስተው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል አሻራውን ለማኖር እንዲዘጋጅ ጥሪ አቅርበዋል። የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ልማት በሀገር አቀፍ ደረጃ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን ተከትሎ በአማራ ክልልም ተጀምሯል። በክልሉ በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞንና በባህርዳር ከተማ አስተዳደር የችግኝ ተከላ መከናወኑን አስታውሰው በሌሎች አካባቢዎችም በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን የሰከላ ወረዳ አርሶ አደር ገደፋዬ ሞገስ እና በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የጓጉሳ ወረዳ አርሶ አደር አለማሁ አድማስ፤ የተራቆቱ አካባቢዎችን በመትከልና በመንከባከብ የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ ተናግረዋል። ጥቅሙን በአግባቡ በመረዳቸው በዘንድረው የክረምት ወቅትም የሚተክሏቸውን ችግኞች በባለቤትነት ተንከባክበው ለማሳደግ መዘጋጀታቸው አስታውቀዋል። በክልሉ ባለፈው ዓመት የክረምት ወቅት ከተተከሉት ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ከ82 በመቶ በላይ መፅደቁን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የአገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ-ኢንስቲትዩቱ
Jul 2, 2025 77
አዲስ አበባ፤ሰኔ 25/2017(ኢዜአ):-በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የአገሪቱ አካባቢዎች ብዙ ቦታዎች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት አስር ቀናት ለክረምት ዝናብ መፈጠር ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ይበልጥ እየተስፋፉና እየተጠናከሩ ይቀጥላሉ። በደቡብ ምዕራብ፣ምዕራብ፣ሰሜን ምዕራብ፣ሰሜን፣ መካከለኛው እና ሰሜን ምስራቅ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት እንደሚኖር አሃዛዊ የትንበያ መርጃዎች እንደሚያሳዩ ተጠቁሟል። በተለይ በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ሰሜን ምዕራብና መካከለኛ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ ብለዋል። አልፎ አልፎ በውሃ አካላትና አካባቢ በምዕራብ፣ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን ምስራቅ እና መካከለኛው የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ በ24 ሰዓት ውስጥ ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ሊኖራቸው እንደሚችል ገልጸዋል። በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ነጎድጓዳማና በረዶ አዘል ዝናብ እና የዝናቡ ጥንካሬም ለረጅም ሰዓታት ያለማቋረጥ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል በመግለጫው ተመላክቷል። በክረምቱ ወቅት የሚዘንበው ዝናብ በአመዘኙ አዎንታዊ ሚና የሚኖረው መሆኑ ተገልጿል። ይህም አስቀድሞ ለተዘሩ ሰብሎች፣ ለመኽር ሰብሎች፣ ለቋሚ ተክሎችና የጓሮ አትክልት የውሃ ፍላጎት ለማሟላት በኩል መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል። አብዛኛው የአገሪቱ ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ የገጸ ምድር የውሃ ፍሰት ይኖራቸዋል፤ነገር ግን አልፎ አልፎ የሚኖረው ከባድ ዝናብ ጎርፍ ሊያስከትል ስለሚችል ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ተመላክቷል። በሌላ በኩል በመጪው አስር ቀናት የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር፣ በምስራቅ አማራ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ምዕራብ እና ደቡብ ምስራቅ የአገሪቱ ሥፍራዎች ላይ ከ26 እስከ 41 ዲግሪ ሴልሺዬስ በላይ ሙቀት እንደሚኖራቸው ትንበያው ያሳያል።
በአረንጓዴ አሻራ በንቃት በመሳተፍ ሌሎች የማህብረሰብ ክፍሎች ተሳትፏቸውን እንዲያጠናክሩ እንሰራለን -የምክር ቤት አባላት
Jul 2, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦በእረፍት ጊዜያቸው ወደ ተመረጡበት አካባቢ ሲሄዱ በአረንጓዴ አሻራ በንቃት በመሳተፍ ሌሎች የማህብረሰብ ክፍሎች ተሳትፏቸውን እንዲያጠናክሩ አበክረው እንደሚሰሩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል። "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ይሆናል። ይህንን ተከትሎ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር መካሔድ ጀምሯል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት አረንጓዴ አሻራን አስመልክቶ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየትም ዜጎች በአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር በመሳተፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገውን ጥረት የበኩላቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ዜጎች በአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር እያደረጉ ያለውን ተሳትፎ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ አባላቱ በእረፍት ጊዜያቸው ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን በአካባቢያቸው በአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል አዲሷ አሰፋ እንደገለጹት፤ ችግኝ መትከል ከሚሰጠው ዘርፈ ብዙ ጥቅም በተጨማሪ ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ ትልቅ ጠቀሜታ አለው፡፡ በመሆኑም ማህበረሰቡ በአረንጓዴ አሻራ ላይ ያለውን ተሳትፎ ይበልጥ በማጠናከር ውጤቱን ማሳደግ እንደሚገባም አመልክተዋል፡፡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ኡስታዝ ካሚል አሊ በበኩላቸው፤ አረንጓዴ አሻራ ለሁለንተናዊ አገራዊ እድገት ወሳኝ በመሆኑ ዜጎች በአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር ላይ ተሳትፏቸውን ማጠናከር አለባቸው ብለዋል፡፡ በዚህ ረገድ በቀጣይ ወደ ተመረጡበት አካባቢያቸው ሲመለሱ ከተጣለባቸው ኃላፊነት ጎን ለጎን ህዝቡ በአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር ይበልጥ ተሳትፎ እንዲጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በምክር ቤቱ የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጌ ቁፋ አረንጓዴ አሻራ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ተመናምኖ የቆየውን የደን ሃብት ወደ ነበረበት በመመለስ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። በመሆኑም ህዝቡ በአረንጓዴ አሻራ ላይ ያለውን ተሳትፎ እንዲጨምር ህዝቡን በማስተባበርና አብሮ በመትከል አገራዊ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ባለፉት አመታት በተከታታይ ተግባራዊ በተደረገው በአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር እየተገኙ ያሉ ውጤቶችን ዘላቂ ማድረግ የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት ነው ያሉት ደግሞ በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ሙሉነሽ ነሞሬ ናቸው። በመሆኑም ማህበረሰቡ ለአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር ያለውን ተነሳሽነት በመጨመር ያለውን ተሳትፎ እንዲያጎላ ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 567
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ። በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1120
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 807
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል። ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1432
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
የህንድ የፈጠራ ማዕከል - ባንጋሎሩ
Jul 2, 2025 93
ቤተልሄም ባህሩ(ኢዜአ) የዴልሂና አግራ ቆይታችንን ጨርሰን ወደ ቀጣይ መዳረሻችን ባንጋሎሩ ከተማ ልንጓዝ ስንሰናዳ አብዛኛው የጋዜጠኛ ልዑክ ያሳሰበው እንደሰም የምታቀልጠውን የአግራ ፀሀይና ሙቀት በባንጋሎሩም ታገኘን ይሆን? የሚለው ነበር። ሆኖም ከዴልሂ ኢንድራ ጋንዲ አየር ማረፊያ ተነስተን ለሶስት ሰዓት ከተቃረበ በረራ በኋላ ያገኘናት ባንጋሎሩ የተለየች ሆነን አገኘናት። ባንጋሎሩ ቀዝቀዝ ባለ አየር ነበር እንግዶቿን የተቀበለችን። በዕለቱ ከክፍሎቻችን ወጥተን በጋራ ወደአየር ማረፊያ የሚወስደንን ትራንስፖርት ስንጠባበቅ ከጋዜጠኛ ቡድኑ ስድስት አባላት ከአጠገባችን እንዳልነበሩ አስተዋልን። የት ጋር እንደተነጣጠልን አላስታውስም። በዚህ ምክንያት ግን የእለቱ ጉዟችን ተሰርዞ ከተማዋን ለማየት ስንዘዋወር የማውቀው ዓይነት እንጂ የተለየ ሙቀት አላስተናገድኩም። የ13 ወር ፀጋ በመባል የምትታወቀው አገሬ ኢትዮጵያ ከዳሎል እስከ ራስ ዳሽን ባላት የመልከዓ ምድር አቀማመጥና ልዩ ልዩ የአየር ጠባይ ሙቀቱንም፣ ቅዝቃዜውንም ማወቃችን እንደዚህ ለአለ አጋጣሚ መልካም ስሜት ይፈጥራል። በተወሰነ ደረጃ በህንድ ያጋጠመኝ የአየር ባህሪ ከአገሬ ጋር ቢመሳሰልብኝ የፈጣሪንና የተፈጥሮን ስራ አጃኢብ ብዬ እንዳልፍ አድርጎኛል። ባንጋሎሩ ከተማ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የህንድ ሲልከን ቫሊ በመባል ትታወቃለች። ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎችም ከመገለጫዎቿ መካከል ናቸው። የጠፈር ጠበብቶቹ - ባንጋሎሩ ደርሰን በመጀመሪያ ያየነው ዓለም በስፔስ ሳይንስ እየሰራች ያለችውና እያስመዘገበችው የምትገኘው ውጤት ማሳያ የሆነውን የህንድ ስፔስ ምርምር ድርጅትን ነው። ተቋሙ የህንድ መንግስት የስፔስ ዲፓርትመንት አካል ሲሆን፤ ዶክተር ቪክራም ሳራብሃይ በተሰኙ ባለራዕይ በ1962 የተወጠነና አሁን ላይ በዘርፉ ተገዳዳሪ መሆን የቻለ ነው። የተቋሙ ዓላማ የስፔስ ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመተግበር ለተለያዩ አገራዊ ጥቅሞች ማዋል መሆኑን ተከትሎ የሳተላይት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማምረት ስራን ጨምሮ ከአገሩ አልፎ ለሌሎች አገራትም በዘርፉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። የተደረገልን ገለፃ አብዛኛውን ጋዜጠኛ ያስደመመ ነበር ከገለፃ በኋላ በጋዜጠኞች የተነሳው ሃሳብም ህንድ በስፔስ ዘርፍ ያላት ልምድና ያከናወነችው ተግባር በቀጣይም ልትሰራ የወጠነቻቸው ሃሳቦች የአገሪቱን መዳረሻ የተለሙ በአገራቸው እንዲተገበር የሚናፍቁት መሆኑን ነው። ተቋሙ በዘርፉ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን የሚያጠናክር መሆኑን ከተደረገልን ገለፃ ተገንዝበናል። በሳይንስ፣ ኢንጂነሪንግና አስተዳደር ምሁራንን በማስተማር እያበረከተ ያለው የህንድ የሳይንስ ኢንስቲትዩት በባንጋሎሩ ከጎበኘናቸው መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የተውጣጡ ተማሪዎችን የሚያስተምርና ከተቋማት ጋርም በዘርፉ የሚሰራ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ከጅማ፣ በተግባር ለመቀየር ሲታትሩ የስታርት አፖችን የምርት ውጤቶቻቸውን ሲፈትሹና ሲሞክሩ ተመልክቻለሁ። በኢትዮጵያም አሁን ላይ ለስታርት አፖች በተሰጠው ትኩረትና በተፈጠረው ምቹ ስነ ምህዳር የፈጠራ ውጤቶች እያደጉና እየተበራከቱ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። እንደ አዳማና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት የተማሪዎችን ፈጠራ ወደ ውጤት ለመቀየር እየተጉ መሆኑና የስታርት አፕ ኤግዚቢሽንና የሰመር ቡት ካምፖች ፈጠራን ምን ያህል እያበራከቱ መሆናቸው በጉብኝቱ ወቅት ወደ አዕምሮዬ የመጣ የአገሬው ህዝብ በውጤት የታጀበ ጥረት ነው። ከአራት አስርት ዓመታት በላይ በባዩቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘው ባዮኮንም ከባላንጎሩ የጉብኝት መዳረሻችን መካከል የሆነና አስፈላጊ መድሀኒቶችን የሚያመርትና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይም እየሰራ ያለ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተጠቃሚ ናቸው። ከ120 በላይ በሆኑ አገራት ለስኳርና ካንሰር ህመም የሚያገለገሉ መድሀኒቶችን በማምረትና በማሰራጨት ለህሙማን ፈውስና ለጤናው ዘርፍ ስርዓት አስተዋፅኦ እያበረከተም ይገኛል። የተቋሙ ላቦራቶሪና ዘመኑን የዋጀና ደረጃውን የጠበቀ ማምረቻ ፋብሪካን መጎብኘቴ አለም በፋርማሲዩቲካልስ ዘርፍ ያለችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። የባንጋሎሩ ቤተመንግስት - ይህን ቤተ መንግስት ማስቃኘቴን ከመጀመሬ በፊት በስፍራው ካስገረመኝ ነገር ላወጋችሁ ወደድኩ። ቤተ መንግስቱን ለመጎብኘት ያቀናነው በእለተ ሰኞ ነበር። ሆኖም ምድረ ግቢውን ቃኝተን ስለህንፃው ሰምተን ከመመለስ ውጪ ወደ ውስጥ አልዘለቅንም። ለምን? ለሚለው ምላሹ በዚህ ስፍራ "ሰኞ የእረፍት ቀን ናት" ነው። እንዴት ካላችሁ ቤተ መንግስቱ ቅዳሜና እሁድ በበርካታ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑን ተከትሎ በስፍራው ለሚሰሩ ሰራተኞች የእረፍት ቀናቸው ሰኞ በመሆኑ ነው። የቤተ መንግስቱ ምድረ ግቢ ሰፊና ልምላሜ የተላበሰ ሲሆን፤ የሚያምርና ለዓይን የሚስብ ኪነ ህንፃ ያለው ነው። አሰራሩና ውጥኑም እንደሚከተለው ነው። በዎዲየር ስርወ መንግስት ንጉስ ቻማራጃ ዋዲያር ወደ እንግሊዝ ባደረጉት ጉዞ በለንደን ዊንሶር ግንብ ይደነቃል። ተደንቆም አልቀረ የባንጋሎሩ ቤተ መንግስትን በተመሳሳይ ሁኔታ ይገነባል። ይህ ቤተ መንግስት በተወሰነ መልኩ የመካከለኛው ዘመን የኖርማንሲና የእንግሊዝ ግንቦችን ይመስላል። ቪድሃና ሶውዳ የካራንታካ ህግ አውጪ አካል መናገሻ በጉብኝታችን ያየነው ሌላው መዳረሻ ስፍራችን ነው። የህግ አውጪና የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የያዘው ይህ ህንፃ ህንድ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ በራሷ መሀንዲስ የሰራችው የመጀመሪያው ህንፃ መሆኑ ተገልፆልናል። የህንፃ ግንባታ ጥበብ ማሳያ፣ የፖለቲካ መናገሻ እንዲሁም የባህል ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። እንደአጠቃላይ በቆይታዬ የተመለከትኩት የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ማበረታቻ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራ ኢትዮጵያ እያከናወነች ካለው የኮሪደር ልማትና ስታርት አፕን የማበረታታት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ምቹነት ስራዎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ነው። በህንድና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ዘመናትን የተሻገረ፤ ለሁለት ሺህ ዓመታት የዘለቀ መሆኑን የታሪክ መዛግብት ያሳያል። የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት በአክሱም ስርወ መንግስት ኢትዮጵያና ህንድ በአዱሊስ ወደብ በኩል የንግድ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያ ቅመማ ቅመምና ሐርን ከህንድ ትገበይ ነበር። ህንድ ደግሞ ወርቅና የዝሆን ጥርስን ከኢትዮጵያ ትሸምት ነበር። ህንድ ከንግድ ልውውጥ ባሻገር በኢትዮጵያ ኪነ ህንፃ ግንባታ ላይ አሻራዋን አኑራለች። በኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍም ትልቅ አበርክቶ ያላት አገር ናት። ህንድ ነፃነቷን ካገኘችበት እኤአ 1948 አንስቶ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት ኢትዮጵያና ህንድ ሌላው የሚያመሳስላቸው ነገር ሆኖ ያገኘሁት የአምራች ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያከናወኑ ያሉት ንቅናቄ ነው። ህንድ እ.አ.አ ከ2014 ጀምሮ የአምራች ዘርፉን ለማበረታታት "ሜድ ኢን ኢንዲያ" በሚል ለአስር ዓመት የተገበረችውና በርካታ ለውጥ የተመዘገበበት ንቅናቄ በኢትዮጵያ ከ2014ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ካለውና የሃገር በቀል ምርቶች እና አምራቾችን ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪያል ማህበረሰብ ግንባታን ማሳደግ ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢ መፍጠር እና የጥናት እና ምርምር ችግር ፈቺነትን ማሳደግን ዓላማ ካደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጋር የተመሳሰለ ነው። ንቅናቄ በኢትዮጵያ መተግበሩ ዓመታዊ የዘርፍ ዕድገት፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና ገቢ ምርት በመተካት በኩል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑም ይታወቃል። በህንድ ተዘዋውሬ በተመለከትካቸው ከተማዎች ባሉ ጎዳናዎች ከታዘብኩት ነገር ሰዎች ከሱቅ ለሚገበያዩት ነገር ሳይቀር በዲጂታል መንገድ ክፍያ መፈፀማቸውን ነው። በባጃጅና በሞተር የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘትም ጭምር ሞባይሉን በመጠቀም “ይህ ቦታ የት ነው?” ሳይል ያሻዎት ስፍራ መድረስም ሌላው ትዝብቴ ነው። ይህ ነገር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትኩረት አግኝተው እየተሰራባቸው ካሉት የዲጂታል ክፍያና ዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ መርሃ ግብር ጋር የሚመሳሰል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በቆይታችን ልክ እንደአትሌቶቻችን ሁሉ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርጎ የሚያስነሳውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝናና ክብር ለማስተዋል ችያለሁ። ፀጉረ ልውጥ መሆናችንን የተገነዘቡ በገበያ ማዕከላት የሚያገኙን እንዲሁም በምንጎበኛቸው ተቋማት የምንተዋወቃቸው ህንዳውያን "ከየት ናችሁ?" ብለው ሲጠይቁ፤ ለእኔና አንድ ከሌላ መገናኛ ብዙሃን የሄድን "ከኢትዮጵያዊ" ስንል የሚከተልልን ምላሽ "አሃ የኢትዮጵያ አየር መንገድ" የሚል ነው። ይህም አየር መንገዱ ስሙ ከኢትዮጵያ ተሰናስሎ የሚጠራ የአገሪቷ መታወቂያ ተቋም መሆኑን ያስገነዘበኝ ነው። ከህንዳውያን ጋር ብቻ ሳይሆን አብረን ከተጓዝን ጋዜጠኞች አንዱ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእናንተ የብቻ ሳይሆን እኛንም እንደራሳችን ሆኖ እያገለገለን ያለ የጋራ አየር መንገዳችን ነው" ሲል ነው የገለፀው። ይሄ ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገር ኩራት ብቻ ሳይሆን መለያ ምልክትም ጭምር መሆኑን የተረዳሁበት አጋጣሚ ነው። በቀናት ቆይታዬ በእንግዳ አክባሪነታቸውና በለገሱን ፍቅርና እንክብካቤ ከአገሬ የራቅኩ ያህል ሳይሰማኝ ብቸኝነትን ሳላስተናግድ እንደውም እየናፈኳቸው እንድመለስ ላደረጉኝ ህንዳውያን በከበረ ሰላምታ ላመሰግን እወዳለሁ።
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 285
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል። ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል። የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው። የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው። ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 831
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች። የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች። ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ። ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 946
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 3049
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት
Dec 16, 2024 2590
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2798
የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል። ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 3915
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2380
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2215
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3653
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል። በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል። የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
መጣጥፍ
የዋጋ ንረት ምን ማለት ነው?
Jun 30, 2025 206
የዋጋ ንረት በንፅፅር ለምሳሌ አምና 26 በመቶ ዘንድሮ 14 በመቶ ሲሆን ምን ማለት ነው? ለምሳሌ የአንድን የ100 ብር ዕቃ ወስደን ብንመለከት ካቻምና ከነበረበት 100 ብር አምና 126 ብር ሆኖ ነበር ማለት ነው። ስለዚህ የዕቃው ዋጋ በአመት ብር 26 ጨምሯል ማለት ነው። በተመሳሳይ መንገድ አምና 100 ብር ዋጋ ያለው ዕቃ ዘንድሮ 14 በመቶ ካደገ ዘንድሮ 114 ብር ይሆናል ማለት ነው። በዚህ ስሌት የዕቃው ዋጋ ካምና ወደ ዘንድሮ የጨመረው በ14 ብር በመሆኑ አምና ከጨመረበት ብር 26 ጋር ሲነፃፀር ጭማሪው ቀንሷል ማለት ነው። ዋጋን ያየን እንደሆነ ግን 100 ብር የነበረ ዕቃ 114 በመሆኑ ጨመረ እንጂ አልቀነሰም። የዋጋ ንረት ጨመረ የሚባለው ደግሞ ለምሳሌ አምና 26 በመቶ የጨመረው ዘንድሮ 14 በመቶ ሳይሆን 30 በመቶ ቢሆን የጨመረው አምና 100 ብር የነበረው ዕቃ ዘንድሮ 114 ሳይሆን 130 ብር ይሆናል ማለት ነው። ይህ አምና ከጨመረበት የ26 ብር ይበልጣል ማለት ነው። ስለዚህ ካቻምና 100 ብር የነበረው ዕቃ አምና 26 ብር ጨምሮ 126 ከሆነ በኋላ ዘንድሮም 14 ብር ስለጨመረ በቀላል ቀመር ዘንድሮ 140 ብር ሆኗል ማለት ነው። ስለዚህ በሁለት አመታት የዕቃው ዋጋ 40 ብር ጨምሯል። የዕቃው ዋጋ አልቀነሰም በየአመቱ የጨመረበት ምጣኔ ግን ካምና ዘንድሮ ያነሰ ነው። ይህ ነው የዋጋ ንረት ቀነሰ ማለት። ዋጋ ቀነሰ ማለትስ ምን ማለት ነው? ዋጋ ቀነሰ የሚለውን ከማየት በፊት የዋጋ ንረት የለም ማለት ምን እንደሆነ በዛው 100 ብር ዋጋ ባለው ዕቃ እንመልከት። ይህ ባለፈው አመት ብር 100 የነበረ ዕቃ ዘንድሮም እዛው 100 ብር ላይ ቢቆይ የዋጋ ንረት ዜሮ ነው። ስለዚህ የዕቃው ዋጋ አልተለወጠም ማለት ነው። ዋጋ ቀነሰ ማለት ግን የዋጋ ንረት ከዜሮ በታች ይሆናል ማለት ነው። በምሳሌው ለማስረዳት አምና 100 ብር ዋጋ ያለው ዕቃ ዘንድሮ 90 ብር ቢሆን የዋጋ ንረቱ ወይም ለውጡ ከዜሮ በታች 10 በመቶ ነው። በዚህ ግዜ የዋጋ ንረት ቀነሰ ሳይሆን ዋጋ ቀነሰ ይባላል። እነዚህ ሶስቱ የዋጋ ለውጦች ለሸማቾችና ለአምራቾች ምን ማለት ናቸው? ለሸማቾች ከሁሉም የሚመረጠው ዋጋ ሲቀንስ ማለትም 100 ብር የነበረው ዕቃ 90 ብር ሲሆን ነው። በሁለተኛ ደረጃ ተመራጩ ዋጋ ንረት ሳይኖር አምና 100 ብር የነበረው ዕቃ ዘንድሮም ሳይለወጥ በዜሮ ንረት 100 ብር ላይ ሲቆይ ነው። ሶስተኛው የተሻለ አማራጭ አምና 100 ብር የነበረ ዕቃ ዘንድሮ በ26 በመቶ ጨምሮ ብር 126 ከሚሆን በ14 በመቶ ጨምሮ ብር 114 ሲሆን ነው። ይህ ሶሰተኛው አማራጭ በሁለቱም ዋጋ ስለሚጨምር በትንሽ የጨመረው ተመራጭ ይሆናል ማለት ነው። ከአምራቾች አንፃር ሲታይ ከላይ ለሸማቾች የተሻለ አማራጭ በቅደም ተከተል ያስቀምጥነውን ገልብጠው ማንበብ ነው። አሁን ብሔራዊ ባንክ እያለ ያለው የዋጋ ንረት ወይም አመታዊ ጭማሪው ቢበዛ ከ10 በመቶ እንዳይበልጥ የሚረዳ የገንዘብ ፖሊሲ እተገብራለሁ ነው። የባንኩ አላማ የዋጋ ንረት ዜሮ ወይም ከዜሮ በታች እንዲሆን ሳይሆን 1) ከ10 በመቶ በታች እንዲሆን ሲሆን 2) የትረጋጋና ተገማች እንዲሆን ነው። የተረጋጋ ማለት ከወር ወር ወይም ካመት አመት ዋጋ የሚለወጥበት ሁኔታ በጣም የተራራቀ ያልሆነ ማለት ነው። ለምሳሌ ካንዱ ወር ወደ ቀጣይ ወር ጭማሪው 0.5 በመቶ ሆኖ በቀጣይ ወር ደግሞ የ5 በመቶ ጭማሪ ከዚያም በቀጣይ ወር ከዜሮ በታች የ2 በመቶ ወርሃዊ ለውጥ ቢመዘገብ ያልተረጋጋ ወይም ተገማች ያልሆነ የዋጋ ለውጥ አለ ማለት ነው። ሰለዚህ የተረጋጋና ተገማች የዋጋ ለውጥ እንዲኖር ማድረግ የባንኩ ሁለተኛው አላማ ነው ማለት ነው። ብሔራዊ ባንክ በጣም ዝቅተኛ የዋጋ ንረት ወይም ከዜሮ በታች የዋጋ ለውጥ እንዴት ያየዋል ብለን ያየን እንደሆነ ነገሩ እንዲህ ነው። ቅድም ከላይ እንዳየነው የዋጋ ንረት ከሸማቾችና ካአምራቾች አንፃር የሚታየው በተቃራኒ መንገድ ነው። ስለሆነም ምንም እንኳን የዋጋ ንረት በጣም ዝቅተኛ ወይም ከዜሮ በታች ቢሆን ለሸማቾች ጥሩ ቢሆንም አምራቾችን ግን የማያበረታታ ስለሚሆን ማምረት ያቆማሉ ሠራተኛ ይቀንሳሉ አጠቃላይ የኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ይገታና ጭራሽ ከምርት እጥረት የተነሳ የዕቃዎች ዋጋ መናር ይከሰታል ሥራ አጥነት ይበዛል። ስለዚህ መንግስት ሥራ እንዲፈጠር ኢኮኖሚ እንዲነቃቃም ስለሚፈለግ የተረጋጋና ዝቅተኛ ሸማቹን የማይጎዳ አምራቹንም የሚያበረታተ የዋጋ ሁኔታ እንዲኖር ይሰራል ማለት ነው። ለአንድ ኢኮኖሚ ትክክለኛው የዋጋ ንረት ስንት ነው? ይህ ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ግን ከባድ ነው። ይህን ጥያቄ ለመመለለስ ከሚረዱት ሁኔታዎች አንዱ ኢኮኖሚው ያለበት ደረጃ ነው። ምን ማለት ነው በጣም ባደገና የበለጠ የማደግ እድሉ ጠባብ ለሆነ ኢኮኖሚ 1 በመቶ ወይም 2 በመቶ የዋጋ ንረት ከፍተኛ ሊሆን ይችላል። በአንፃሩ ደግሞ ገና የማደግ እምቅ አቅም ላለውና በማደግ ላይ ላለ ሀገር ነጠላ አሃዝ የዋጋ ንረት እንደ ሁኔታው የሚለያይ ሆኖ ተመራጭ ሊሆን ይችላል። ስንት ነው የሚለው ግን በሳይንሳዊ መንገድ መረጋገጥ አለበት። ለምሳሌ የሀገራችንን threshold inflation or optimal inflation level ለማወቅ እኔን ጨምሮ የባንኩ ሠራተኞች በሳይንሳዊ መንገድ ለማወቅ ተሞክሯል። በኔ ጥናት 7 በመቶ ሲሆን በሌሎቹም ከዚሁ ያልራቀ ውጤት እንዳለ አይቻለው የመረጃ አጠቃቀምና የሜቶዶሎጂ ልዩነቱ እንዳለ ሆኖ ማለቴ ነው። ሰለዚህ በነዚህ ጥናት መሰረት ብሔራዊ ባንክ የነጠላ አሃዝ የዋጋ ንረት አላማ አድርጎ መንቀሳቀሱ ትክክለኛ አቅጣጫ ነው ማለት ነው ለኛ ኢኮኖሚ። ለማጠቃለል የዋጋ ንረት ምንነትን በተመለከተ ያለውን ውዥምብር ለማጥራት ይህ አጭር መግለጫ ያግዛል ብዬ እያመንኩ የበለጠ መብራራት ካለበት ወይም ጥያቄ ካለ አንባቢዎች በአስተያየት መስጫው ላይ ማሰቀመጥ ትችላላችሁ። አቶ ፈቃዱ ደግፌ የብሔራዊ ባንክ ም/ገዥ
የሺህ ሀይቆች ምድር
Jun 24, 2025 458
የሺህ ሀይቆች ምድር (በራሔል አበበ) በርካታ መገለጫዎች አሏት። የሺህ ሀይቆች መፍለቂያ። አረንጓዴ ምድር። 75 በመቶ የአገሪቱ ገፀ-ምድር በደን የተሸፈነ። የአምስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ሕዝብ መኖሪያ። በአውሮፓ ከበለጸጉ አገራት አንዷ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለስምንት ተከታታይ ዓመታት በዓለም ቁጥር አንድ የደስተኞች አገር በመባል የተሰየመች ሰሜን አውሮፓዊት አገር - ፊንላንድ። በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋባዥነት በአዲስ አበባ የአገሪቱ ኤምባሲ አስተባባሪነት በቅርቡ ፊንላንድን የመጎብኘት ዕድል አግኝቼ ነበር። በጉብኝቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ የኬኒያ፣ ታንዛኒያ፣ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴኔጋል፤ ሞዛምቢክ እና ዛምቢያ ጋዜጠኞች ተሳትፈናል። የአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ነው። ምንም እንኳን የትም አገር ስሄድ ቀድሜ መረጃ የማየት ልምድ ቢኖረኝም በመጀመሪያው ዕለት ለእራት ስንወጣ ያየሁት በምሽት ያልተለመደ የፀሐይ ፍካት ግን እራቱ ቁርስ እንዲመስለኝ አድርጓል። ከዚያ በኋላ ለመድሁት። በእርግጥ በአንድ ወቅት በስፔንም ፀሐይ እስከ እኩለ ሌሊት የማትጠልቅበትን ክስተት ተመልክቻለሁ። በፊንላንድ ያየሁት ግን ተለየብኝ። ፀሐይ ፈጽሞ ለጨረቃ ቦታ መልቀቅ አትፈልግም። ምሽቱ የሚደምቀው በመብራት ሳይሆን በፀሐይ ነው። ሌሊቱ ብርሀን ነው። ሰማይ አይጠቁርም። በየዕለቱ ሳይጨልም ይነጋል። በዚህ ወቅት በተለያዩ የአውሮፓና የአሜሪካ አገራት ሰማይ ላይ የሚታየው ሰሜናዊ የቀለማት የብርሀን ፀዳል ሌላው የፊንላንድ መድመቂያ ነው። የሰሜን አውሮፓ/ኖርዲክ አገራት በተፈጥሮ የታደሉ ናቸው። እኔ ደግሞ የተፈጥሮ አድናቂ ነኝ። ያለማጋነን በፊንላንድ ተፈጥሮ ከነክብሯ ተጠብቃ አይቻለሁ። ንጹህ አየሯ የዚህ ውጤት ነው። አድናቆቴ የጀመረው ከኤርፖርት እስካረፍኩበት ሆቴል 15 ኪሎ ሜትር ያህል በመኪና ስንጓዝ የከተማዋን አረንጓዴነትና የምድሪቱን ልምላሜ ስመለከት ነበር። በጉብኝቴም በተግባር አረጋገጥሁ። የአገሪቱ አብዛኛው መሬት በደንና በውሃ ተሸፍኗል። በዋና ከተማዋ ሄልሲንኪና በዙሪያዋ በሚገኙ ውብ ደኖች መሀል ስንጓዝ መሬቱ ለም ስለመሆኑ ዓይን ብቻ ሳይሆን እግርም ምስክር ነው። ሲራመዱ የመሬቱ ምቾትና እንደ ስፖንጅ ስምጥ ስምጥ ማለት ለምነቱን ይናገራል። በሄልሲንኪ ሴኔት እና ካንሳላስቶሪ አደባባዮች እንደእኛዎቹ አራት እና ስድስት ኪሎ አደባባዮች ናቸው። ቤተ-መንግስት፣ ዩኒቨርሲቲ፣ ፓርላማ፣ ቤተ-መጽሐፍት እና ቤተክርስቲያንን አጎራብተው ይዘዋል። የሄልሲንኪ ሕንጻዎች እንደ ሌሎች የአውሮፓ አገራት ውብና የሥነ-ሕንጻ ጥበብ የሚታይባቸው ናቸው። የነዋሪዎች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ ከተማዋ አልተጨናነቀችም። በአስፋልትና ደረጃውን በጠበቀ ኮብልስቶን የተሰራው የከተማዋ አውራ ጎዳና ከዘመናዊ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ የህዝብ አውቶቡስና የኤሌክትሪክ ባቡር ያስተናግዳል። ለአውሮፓ ከተሞች አዲስ የሆነ ሰው ኮብልስቶኑ የእግረኛ መንገድ መስሎት መሐል የመኪና መንገድ ላይ ሊገኝ ይችላል። እኔም የተረፍሁት እንዲህ አይነቱን የመኪና መንገድ በአንድ ወቅት በኢጣልያ በማየቴ ነበር። የተፈጥሮ ውበት ደምቆ የሚታይባት ፊልናልድ ሲልቨር በርች የተሰኘው ብርማ ቀለም ቅርፊት ያለው ዛፍ እና ቡናማ ድብ ብሔራዊ መለያዎቿ ናቸው። በረጃጅሞቹ ዛፎች መሐል ከእንስሳት ባሻገር ስትሮበሪና እንጉዳይን ጨምሮ ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ዕጽዋት ይገኛሉ። በፊንላንድ ብዙ አይነት የእንጆሪ/ስትሮበሪ ዝርያ አለ። ወቅቱ ፍሬ የሚደርስበት አልነበረም እንጂ ከጫካዎቹ መሐል ገብቶ በተለያዩ የስትሮበሪ ፍሬዎች ቅርጫት ሞልቶ መውጣት የተለመደ መሆኑን ተረድቻለሁ። ፊንላንድ የሺህ ሀይቆች ምድር ተብላም ትሞካሻለች። ለቁጥር የሚያዳግቱ በበርካታ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሀይቆችና የውሀ አካላት ከተፈጥሮ ሀብቶቿ መካከል ናቸው። ለጉብኝት በሄድኩባቸው አካባቢዎች ሁሉ የሚቀርብልኝን ኩልል ያለ ንጹህ የመጠጥ ውሃ በፍቅር ነበር የምጠጣው። ግዴታ ካልሆነ የፋብሪካ ውሃ በፊንላንድ ቦታ የለውም። ንጹህ የተፈጥሮ የምንጭ ውሃ ከቧንቧ ይቀዳል። ጽድት ከማለቱ ጣዕሙ። ፊኒሾች ለባህልና ቅርስ ትልቅ ቦታ አላቸው። በተለይ ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ቁርኝት አስገራሚ ነው። በአብዛኛው አፍሪካ ውስጥ የሚነገር አፈ-ታሪክና ተረት በፊንላንድም ከተፈጥሮ በተለይም ከዛፎችና ከእንስሳት ጋር ተያይዞ ሲተረትና የመድረሻቸው መነሻ እንደሆነ ሲነገር ተደንቄያለሁ። በጉብኝታችን በአንዱ ቀን ኑኪሲኦ ብሔራዊ ፓርክ ሄድን። ይህ ደግሞ እጅግ የተለየ ተፈጥሮን ማያ ስፍራ ነው። በረዣዥም ዛፎች መሐል ካደረግነው ጉዞ በኋላ የቀረበልን ባህላዊው የፊንላንድ የሳውና እና የዋና ግብዣ ነበር። ሳውና የፊንላንድ ባህል ነው። በእንግሊዝኛ ቋንቋ መዝገበ ቃላት ውስጥ ያለ የፊኒሽ ቃል “ሳውና” እንደሆነ ይነገራል። ዛሬ በዓለም ላይ በተለይም በባለኮከብ ሆቴሎች በስፋት የምናገኘው ሳውና መነሻው ፊንላንድ ናት። በርካታ የሳውና ስፍራዎች ከመኖራቸው የተነሳ የሳውና ቁጥር በአገሪቱ ከተመዘገቡ መኪኖች ቁጥር ይበልጣል ይባላል። ግብዣውን ሁላችንም በደስታ ነበር የተቀበልነው። በባህሉ መሰረት ሳውና ውስጥ በቅጠል እየተጠበጠብን ከፍተኛ ሙቀት ሲሰማን ከፊት ለፊት ባለው ቀዝቃዛ የተፈጥሮ ሀይቅ ውስጥ በመግባት ዋና የሚችል ዋኝቶ የማይችል ደግሞ በመነከር ሰውነቱን አቀዝቅዞ እንደገና ወደሳውናው ይመለሳል። የተለየ ነው። የጉብኝቱ ዋና አስተባባሪ አና ላሚላ ትባላለች። የ35 ዓመት የስራ ልምድ ያላት ብስል ዲፕሎማት ናት። በተለያዩ አገራት ፊንላንድን ወክላ ሰርታለች። አሁንም በአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አምባሳደር ነች። ትክክለኛ የኮሙኒኬሽን ሰው ናት። አንቺ ያልኳት በአንቱታ ላርቃት ባለመፈለጌ ነው። ለነገሩ ስትታይም የ35 ዓመት ወጣት እንጂ የ35 ዓመት የስራ ልምድ ያላት አትመስልም። አንድ ቀን አን “መኮንን” በሚለው የአያቴ ስም እየጠራችኝ ስምሽ እኮ የፊኒሽ/የፊንላንድ ነው ይህን ታውቂያለሽ? ከእኛ ጋር ዝምድና ይኖርሽ ይሆን?" አለችኝ ፈገግ ብላ። "ኸረ በፍፁም ኢትዮጵያዊት ነኝ" አልኳት። ትክክል ነበረች። አጭር የፅሁፍ መልዕክት የመለዋወጥ ሀሳብን ለመጀመሪያ ጊዜ ለዓለም ያስተዋወቀው “ማቲ መኮንን” የተባለ ፊንላንዳዊ ኢንጂኒየር ነው። የቴክኖሎጂ ነገር ከተነሳ አብዛኞቻችን ከተንቀሳቃሽ ስልክ ጋር ስንተዋወቅ የያዝነው ኖኪያ የፊንላንድ ምርት ነው። የመኮንንን ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ በተንቀሳቃሽ ስልክ አማካኝነት ለዓለም ይፋ ያደረገውም ኖኪያ ነው። አሁንም ኖኪያ በኔትወርክ ዝርጋታ ጭምር እየሰራ ያለ ግዙፍ የቴሌኮም ተቋም ነው። ኢትዮጵያና ፊንላንድ የረዥም ዓመታት የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው። ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸው 66 ዓመታትን ተሻግሯል። ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ከእርዳታና ትብብር ባሻገር በተለያየ መስክ በጋራ ትሰራለች። በጉብኝቴ ወቅት ያገኘኋቸው የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሌና ቫልቶነን ይህን ግንኙነት የማሳደግ ፍላጎት መኖሩን ነግረውኛል። ከንግድና ኢንቨስትመንት በተጨማሪ ኖኪያን ከመሰሉ ኩባንያዎች ጋር የሚደረግ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና በአገሪቱ ቴክኖሎጂ መዘመኑን የተረዳሁት በአገሪቱ ብሔራዊ የሚዲያ ተቋም ይሌ ያለማንም እርዳታ ዜና ቀርጾ የሚያሰራጭ ሰው አልባ ሮቦትድ የስቱዲዮ ቴክኖሎጂ ስመለከት ነበር። ፊንላንድ በትምሕርት ጥራትም ስሟ በቀዳሚነት ይነሳል። በአገሪቱ ከ800 በላይ፤ በመዲናዋ ደግሞ 40 የሚጠጉ ቤተ-መጻሕፍት አሉ። ከአገሪቱ ፓርላማ አቅራቢያ የሚገኘውና አገሬው የእኩልነት ተምሳሌት ነው የሚለው የሄልሲንኪ ግዙፉ ማዕከላዊ ቤተ-መጽሐፍት ኦዲ ይባላል። በውስጡ በርካታ አገልግሎቶችን ይዟል። ንባብ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ የባህልና ፈጠራ ታለንቶችን ያስተናግዳል። ከልጅ እስከ አዋቂ ለሁሉም ቦታ አለው። ፊንላንድ ዜጎቿ በደስታ ግብር የሚከፍሉባት አገር መሆኗን የአገሪቱ የታክስ አስተዳደር ሲናገር በኩራት ነው። ግብር መሰወር፤ ክፈሉ ብሎ በየግዜው መቀስቀስን የመሳሰሉ ነገሮች እዛ ቦታ የላቸውም። የኩባንያም ሆነ የግለሰብ ግብር ከፋዮች በታማኝነት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በወቅቱ እንደሚወጡ አስተዳደሩ ይገልጻል። ይህም የዜጎች ፍላጎትን ለማሟላት በተሰራ ስራ የተፈጠረ መሆኑን የተመለከትኳቸው ተቋማት ሃላፊዎች ይገልጻሉ። ዜጎች በመንግስት ላይ ከፍተኛ እምነት አላቸው። በፊንላንድ የዜጎች ደስተኝነት የሰላምና ነጻነት መገለጫ እንደሆነ ምሁራኖቻቸው በጥናት ስራዎቻቸው ጭምር ይመሰክራሉ። የደስታቸው ምንጭ ነጻና ጥራት ያለው ትምሕርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፤ በፍትህና እኩልነት፤ በበጎ አድራጎት ተግባር፤ የእናቶችና ህጻናት ጤናን ጨምሮ አርአያ የሚሆኑ ጠንካራ የማሕበራዊ ደህንነትና ትስስር ስራዎች የመጡ ውጤቶች እንደሆኑ ይገለጻሉ። በጾታ እኩልነት ሴቶች በሁሉም መስክ ጥሩ ስፍራ አላቸው። በፖለቲካውም ከወንዶች ተቀራራቢ ቦታ እንዳላቸው የአገሪቱን ፓርላማ ስንጎበኝ ተረድቻለሁ። ከ200 የምክር ቤት አባላት 91ዱ ሴቶች ናቸው። የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ፊንላንድ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደስተኛ አገራት ደረጃ ላይ ለስምንት ተከታታይ ዓመታት የከፍታ ስፍራዋን ሳትለቅ በቁጥር አንድ ላይ እንድትቆይ አድርጓታል። ዜጎቿ በቀጣዩ ዓመትም ለዘጠነኛ ጊዜ የዓለም የደስተኞች አገር ሆና ትቀጥላለች የሚል እምነት አላቸው።