ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ እና ጃፓን በፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች ትብብራቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ መከሩ
Apr 8, 2026 11
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጃፓን በፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች ትብብርና አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ መምከራቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ በጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦው ሳዳማና በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ የተመራ የልዑካን ቡድን ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አብዩ እና ከተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች በተመለከተ የሚደረጉ ትብብሮችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ምክክር ተደርጓል።   ኢትዮጵያና ጃፓን ከዚህ ቀደም በደኅንነትና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ የሚሠሯቸውን ተግባራት በማጠናከር በቀጣናው የሚንቀሳቀሱ ሽብርተኛ ቡድኖችንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል መክረዋል። በሳይበርና በአቪዬሽን ደኅንነት ዙሪያ የሚደረጉትን ትብብሮችና የመረጃ ልውውጦች ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮችም ላይም ተወያይተዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አቢዩ፤ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የተከናወኑ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንዲሁም የፀጥታ ዘርፍ ሪፎርሞችን በተመለከተ ለጃፓን ልዑክ አባላት ገለጻ አድርገዋል። በዚህ ወቅት የሪፎርም ሥራዎቹን ፋይዳም አብራርተዋል፡፡   ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አቢዩ፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ አማራጭ መንገዶች የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን እንቅስቃሴዎች ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል። የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦው ሳዳማና በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ካላት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እና ተጽዕኖ ፈጣሪነት አኳያ የሁለቱን ሀገራት ትብብርና አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ይሰራል፡፡ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመረጃና በልምድ ልውውጥ እንዲሁም በአቅም ግንባታ መስኮች የተጀመሩ የአጋርነት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን ጥረቶች ጃፓን እንድምትደግፍ ገልፀዋል።   የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት ያደነቁት የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር አማካሪ፤ በአጭር ዓመታት ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ ሪፎርምና ትላልቅ የከተማ ልማት ሥራዎችን መሥራቷ ለሌሎች በአብነት የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል።
በገንዳውኃ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ የተከማቸ ከ950 ሊትር በላይ ነዳጅ ተያዘ
Apr 8, 2026 16
ገንዳውኃ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳውኃ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረ ከ950 ሊትር በላይ ነዳጅ መያዙን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ሀይሌ ብርሃኑ 900 ሊትር ናፍጣ እና 56 ሊትር ቤንዚን በግለሰብ ቤት ከተደበቀበት ለመያዝ መቻሉን ገልጸዋል።   በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረው ነዳጅ ሊያዝ የቻለው የጸጥታ አካላት ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻና ጥብቅ ክትትል መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ ነዳጁ በህገወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘው በከተማው ቀበሌ 03 ልዩ ቦታው ቀጠና 08 በተባለ አካባቢ ነው።   በቀጣይም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጫና የሚፈጥሩ መሰል ህገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የቁጥጥር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ህብረተሰቡ ህገ ወጥ ተግባር ተፈጽሞ ሲያይ ለጸጥታ አካላት ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለውን ትብብር በቀጣይም አጠናክሮ እንዲቀጥል ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።
የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በባህር ዳር ከተማ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ የማጋራት ተግባር ተከናወነ 
Apr 8, 2026 57
ባህር ዳር ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ በባህር ዳር ከተማ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መርሀግብር ተከናወነ። የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሰብለ ዘውዱ በማዕድ ማጋራት መርሀግብሩ ላይ እንደገለጹት፣ በዓልን በመደጋገፍ በአብሮነት የማሳለፍ እሴት ተጠናክሮ ቀጥሏል።   በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የተለያዩ አካላትን በማስተባበር አቅመ ደካማ ወገኖች በዓልን ተደስተው እንዲያሳልፉ የተጀመረው የድጋፍ ሥራ ውጤት እየታየበት መሆኑን ተናግረዋል። በዛሬው እለትም ለ400 አቅመ ደካሞች የበዓል መዋያ ድጋፍ መደረጉን ገልጸው፣ በዚህም ለእያንዳንዳቸው የዳቦ ዱቄት፣ የዘይት እና የዶሮ ድጋፍ ተደርጓል ብለዋል። መምሪያው ባለድርሻ እና አጋር አካላትን በማስተባበር ከሚያደርገው ከዕለታዊ ድጋፍ በተጨማሪ ለዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ወይዘሮ ሰብለ አስረድተዋል። ከድጋፉ ተጠቃሚዎች መካከል ወይዘሮ እናት በሽር በሰጡት አስተያየት የተደረገላቸው ድጋፍ በዓሉን ያለሀሳብ ከቤተሰባቸው ጋር ተደስተው ለማሳለፍ እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።   ድጋፍ ላደረጉላቸው አካላት ምስጋናቸውን ያቀረቡት ወይዘሮዋ፣ ድጋፉ ተጠናክሮ ሌሎችም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጠይቀዋል። አቶ አስማረ አያሌው የተባሉ ሌላው የማዕድ ማጋራቱ ተጠቃሚ በበኩላቸው በአቅም ማነስ ለበዓል እየተጨነቁ ባለበት ወቅት የድጋፉ ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውን ነው የገለጹት። በዛሬው እለት የተደረገላቸው የበዓል መዋያ ድጋፍ በዓሉን ከቤተሰባቸው ጋር በአብሮነትና በደስታ ለማሳለፍ እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያና ጃፓን በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Apr 8, 2026 125
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018(ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያና ጃፓን በጋራ ፍላጎቶቻቸውና በጸጥታ ጉዳይ ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦዌ ሳዳማሳ የተመራውን የልዑካን ቡድን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።   በቆይታቸውም የሁለቱን አገራት ብሄራዊ ጥቅሞች፣ የጋራ ፍላጎትና እሴቶችን ባከበሩ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በቅንጅት መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ዙሪያ ተወያይተዋል። ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካም ሆነ በአህጉር ደረጃ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የምታከናውናቸውን ተግባራት ልዩ አማካሪው ኦዌ ሳዳማሳ አድንቀዋል። በተለይም በሰላም ማስከበር ረገድ ያላትን ሰፊ ተሞክሮ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ጃፓን በዚህ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ያላትን ከፍተኛ ፍላጎት አረጋግጠዋል። ጃፓን የኢትዮጵያን የሰላም ማስከበር ማዕከል አቅም ለመገንባት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የጠቆሙት አማካሪው፤ በስልጠና እና በልምድ ልውውጥ የመከላከያ ሰራዊቱን የሰው ኃይል የሙያ ብቃት ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነትም ገልጸዋል።   ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በበኩላቸው፣ ጃፓን ለትብብር ያሳየችውን ተነሳሽነት በማድነቅ፤ ኢትዮጵያ በእውነተኛ ወዳጅነትና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ወታደራዊ አጋርነትን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አመልክተዋል። ይህ ትብብርም በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ያላቸውን እምነት መግለጻቸውን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያሳያል።
የሚታይ
ኢትዮጵያ እና ጃፓን በፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች ትብብራቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ መከሩ
Apr 8, 2026 11
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጃፓን በፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች ትብብርና አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ መምከራቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ በጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦው ሳዳማና በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ የተመራ የልዑካን ቡድን ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አብዩ እና ከተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች በተመለከተ የሚደረጉ ትብብሮችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ምክክር ተደርጓል።   ኢትዮጵያና ጃፓን ከዚህ ቀደም በደኅንነትና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ የሚሠሯቸውን ተግባራት በማጠናከር በቀጣናው የሚንቀሳቀሱ ሽብርተኛ ቡድኖችንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል መክረዋል። በሳይበርና በአቪዬሽን ደኅንነት ዙሪያ የሚደረጉትን ትብብሮችና የመረጃ ልውውጦች ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮችም ላይም ተወያይተዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አቢዩ፤ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የተከናወኑ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንዲሁም የፀጥታ ዘርፍ ሪፎርሞችን በተመለከተ ለጃፓን ልዑክ አባላት ገለጻ አድርገዋል። በዚህ ወቅት የሪፎርም ሥራዎቹን ፋይዳም አብራርተዋል፡፡   ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አቢዩ፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ አማራጭ መንገዶች የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን እንቅስቃሴዎች ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል። የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦው ሳዳማና በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ካላት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እና ተጽዕኖ ፈጣሪነት አኳያ የሁለቱን ሀገራት ትብብርና አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ይሰራል፡፡ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመረጃና በልምድ ልውውጥ እንዲሁም በአቅም ግንባታ መስኮች የተጀመሩ የአጋርነት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን ጥረቶች ጃፓን እንድምትደግፍ ገልፀዋል።   የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት ያደነቁት የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር አማካሪ፤ በአጭር ዓመታት ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ ሪፎርምና ትላልቅ የከተማ ልማት ሥራዎችን መሥራቷ ለሌሎች በአብነት የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያና ጃፓን በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Apr 8, 2026 125
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018(ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያና ጃፓን በጋራ ፍላጎቶቻቸውና በጸጥታ ጉዳይ ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦዌ ሳዳማሳ የተመራውን የልዑካን ቡድን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።   በቆይታቸውም የሁለቱን አገራት ብሄራዊ ጥቅሞች፣ የጋራ ፍላጎትና እሴቶችን ባከበሩ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በቅንጅት መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ዙሪያ ተወያይተዋል። ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካም ሆነ በአህጉር ደረጃ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የምታከናውናቸውን ተግባራት ልዩ አማካሪው ኦዌ ሳዳማሳ አድንቀዋል። በተለይም በሰላም ማስከበር ረገድ ያላትን ሰፊ ተሞክሮ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ጃፓን በዚህ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ያላትን ከፍተኛ ፍላጎት አረጋግጠዋል። ጃፓን የኢትዮጵያን የሰላም ማስከበር ማዕከል አቅም ለመገንባት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የጠቆሙት አማካሪው፤ በስልጠና እና በልምድ ልውውጥ የመከላከያ ሰራዊቱን የሰው ኃይል የሙያ ብቃት ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነትም ገልጸዋል።   ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በበኩላቸው፣ ጃፓን ለትብብር ያሳየችውን ተነሳሽነት በማድነቅ፤ ኢትዮጵያ በእውነተኛ ወዳጅነትና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ወታደራዊ አጋርነትን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አመልክተዋል። ይህ ትብብርም በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ያላቸውን እምነት መግለጻቸውን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያሳያል።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ለአፍሪካ ምሳሌ ናቸው
Apr 8, 2026 123
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ፣ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከልና ምላሽ ለአፍሪካውያን ምሳሌ የሆኑ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት 16ኛው የአፍሪካ አደጋ ሥጋት አቅም አህጉራዊ ጉባኤ "ለሉዓላዊነት መተባበር" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን እየተካሄደ ነው።   39 የአፍሪካ አደጋ ሥጋት አቅም አባል ሀገራትና ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን እየተሳተፉበት የሚገኘው ይህ ጉባኤ፤ በአፍሪካውያን መካከል ትብብርና አጋርነትን በመፍጠር አህጉራዊ የአደጋ ሥጋትን የመከላከልና የፋይናንስ አቅምን ማጠናከርን ያለመ ነው። የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካውያን የምግብ ሉዓላዊነትን በራሳቸው አቅም ለማረጋገጥ ለጋራ ግብ የሚተባበሩበት ወሳኝ ወቅት ላይ ናቸው፡፡ የአፍሪካ የአደጋ ሥጋት አቅም አህጉራዊ የምግብ ሉዓላዊነትን በራስ አቅም ለማሳካት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ የተቀናጀ የአደጋ ሥጋት ምላሽ መስጠት የሚያስችል አህጉራዊ የፋይናንስ አቅም መገንባት ይገባል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ግቦችን በማሳካት የምንመኛትን አፍሪካ ለመገንባት የሀገራት ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነትና ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ስርዓት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ቀዳሚ አጀንዳ መደረጉን ገልጸው፤ ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠር የተሟላ ድጋፍ ማድረግ የሚያስችል አቅም ተገንብቷል ብለዋል፡፡   ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ አረንጓዴ አሻራ፣ መስኖ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የታዳሽ ኃይል እና ሌሎችም ኢንሼቲቮች የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን በመከላከል እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን በመመከት፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥና የአደጋ ምላሽ በመስጠት ለአፍሪካና ለዓለም ምሳሌ እየሆነች ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ያሳየችው ስኬት ጉባኤውን ለማስተናገድ ተመራጭ እንዳደረጋትም ኮሚሽነሩ አንስተዋል። የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም ጉባኤ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም በማሟላትና የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ያስመዘገበቻቸውን ተሞክሮዎች የምታጋራበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ሥርዓት ለመገንባት የተገበረቻቸው ኢኒሼቲቮች የምግብ ሉዓላዊነትን እና የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማሳካት እንደሚያስችሉ ተናግረዋል፡፡ በአዲስ አበባ የሚሰሩ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን መከላከልና የአደጋ ምላሽ በመስጠት ለአፍሪካውያን ምሳሌ የሆኑ የተግባር ማሳያዎች ናቸው ብለዋል፡፡
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ አጋሩ 
Apr 8, 2026 108
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አከናውነዋል። ፕሬዝዳንቱ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ማዕድ ማጋራት በፈጣሪ ዘንድ የተወደደ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቅመ ደካማ ወገኖች በበዓላት ወቅት በራቸውን ዘግተው ማሳለፍ የለባቸውም በሚል የጀመሩት ተነሳሽነት ኢትዮጵያዊ የመረዳዳት ባህል ይበልጥ እንዲዳብር ማድረጉን ጠቅሰዋል። ይህ የመረዳዳት ተግባር በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች በበዓል ወቅት ቤታቸው ባዶ እንዳይሆንና ከሌላው ወገኖች ጋር በጋራ እንዲያሳልፉ የሚያስችል መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።   የመንግስት ዋነኛ ዓላማ ሁሉም ዜጋ ራሱን ችሎ የተሻለ ህይወት እንዲመራ ማስቻል መሆኑን ያመለከቱት ፕሬዝዳንቱ፤ ለዚህም መንግስት በሰው ተኮር ፖሊሲው በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ሰባተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ይካሄዳል
Apr 8, 2026 138
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ሰባተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስን በሚመለከት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኮንፍረንሱ ከሚያዚያ 7 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ጠቁመዋል፡፡ በኮንፍረንሱ ላይ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምን ለማፅናት በሚያስችሉና በሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት የፓናል ውይይት እና ህዝባዊ ውይይት እንደሚካሄድ ገልጸዋል። ከኮንፍረንሱ በተጨማሪ በክልሉ ያሉ የልማት ስራዎች ጉብኝት፣ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብርና ሌሎች የተለያዩ ሁነቶች እንደሚከናወኑ አብራርተዋል። ለሁለት ቀናት በሚኖረው ኮንፍረንስ ላይ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የሃይማኖት አባቶች፣ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚሳተፉም አክለዋል። ጉባኤው ከዚህ ቀደም በተለያዩ ክልሎች ባካሄዳቸው ስድስት የሰላም ኮንፍረንሶች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ አዎንታዊ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። የሃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ለዜጎች የሰላም ጥሪን በማስተላለፍና በማስተማር ለሰላም ዘብ የሆነ ትውልድን ለመፍጠር ትልቅ ሚና መጫወት ችለዋል ብለዋል። ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችም ለስሙነ ህማማት እና ለስቅለት በአል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ኢትዮጵያ እና ጃፓን በፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች ትብብራቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ መከሩ
Apr 8, 2026 11
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጃፓን በፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች ትብብርና አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ መምከራቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ በጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦው ሳዳማና በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ የተመራ የልዑካን ቡድን ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አብዩ እና ከተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች በተመለከተ የሚደረጉ ትብብሮችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ምክክር ተደርጓል።   ኢትዮጵያና ጃፓን ከዚህ ቀደም በደኅንነትና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ የሚሠሯቸውን ተግባራት በማጠናከር በቀጣናው የሚንቀሳቀሱ ሽብርተኛ ቡድኖችንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል መክረዋል። በሳይበርና በአቪዬሽን ደኅንነት ዙሪያ የሚደረጉትን ትብብሮችና የመረጃ ልውውጦች ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮችም ላይም ተወያይተዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አቢዩ፤ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የተከናወኑ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንዲሁም የፀጥታ ዘርፍ ሪፎርሞችን በተመለከተ ለጃፓን ልዑክ አባላት ገለጻ አድርገዋል። በዚህ ወቅት የሪፎርም ሥራዎቹን ፋይዳም አብራርተዋል፡፡   ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አቢዩ፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ አማራጭ መንገዶች የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን እንቅስቃሴዎች ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል። የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦው ሳዳማና በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ካላት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እና ተጽዕኖ ፈጣሪነት አኳያ የሁለቱን ሀገራት ትብብርና አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ይሰራል፡፡ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመረጃና በልምድ ልውውጥ እንዲሁም በአቅም ግንባታ መስኮች የተጀመሩ የአጋርነት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን ጥረቶች ጃፓን እንድምትደግፍ ገልፀዋል።   የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት ያደነቁት የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር አማካሪ፤ በአጭር ዓመታት ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ ሪፎርምና ትላልቅ የከተማ ልማት ሥራዎችን መሥራቷ ለሌሎች በአብነት የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያና ጃፓን በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Apr 8, 2026 125
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018(ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያና ጃፓን በጋራ ፍላጎቶቻቸውና በጸጥታ ጉዳይ ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦዌ ሳዳማሳ የተመራውን የልዑካን ቡድን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።   በቆይታቸውም የሁለቱን አገራት ብሄራዊ ጥቅሞች፣ የጋራ ፍላጎትና እሴቶችን ባከበሩ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በቅንጅት መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ዙሪያ ተወያይተዋል። ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካም ሆነ በአህጉር ደረጃ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የምታከናውናቸውን ተግባራት ልዩ አማካሪው ኦዌ ሳዳማሳ አድንቀዋል። በተለይም በሰላም ማስከበር ረገድ ያላትን ሰፊ ተሞክሮ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ጃፓን በዚህ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ያላትን ከፍተኛ ፍላጎት አረጋግጠዋል። ጃፓን የኢትዮጵያን የሰላም ማስከበር ማዕከል አቅም ለመገንባት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የጠቆሙት አማካሪው፤ በስልጠና እና በልምድ ልውውጥ የመከላከያ ሰራዊቱን የሰው ኃይል የሙያ ብቃት ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነትም ገልጸዋል።   ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በበኩላቸው፣ ጃፓን ለትብብር ያሳየችውን ተነሳሽነት በማድነቅ፤ ኢትዮጵያ በእውነተኛ ወዳጅነትና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ወታደራዊ አጋርነትን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አመልክተዋል። ይህ ትብብርም በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ያላቸውን እምነት መግለጻቸውን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያሳያል።
ወጣቶች በምርጫ ላይ በንቃት በመሳተፍ ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ መጎልበት ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው  
Apr 8, 2026 189
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ መጎልበት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባችው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አህመድ ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር "በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የወጣቶች ድምፅና ተሳትፎ ለሠላምና ለዴሞክራሲ“ በሚል መሪ ሀሳብ የወጣቶች ተሳትፎን ለማጎልበት ያለመ የንቅናቄ መርሃ ግብር አካሂዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አህመድ እንደገለጹት፤ ወጣቶች የዲሞክራሲያዊ ስርዓቱ ዋነኛ ምሰሶ በመሆናቸው በምርጫ ሂደቱ ንቁ ተሳታፊ ሊሆኑ ይገባል። በዚህም የሀገሪቱን የልማትና የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ጉዞን ለማፋጠን እንደሚቻል ጠቁመው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በወጣቶች ሙሉ ተሳትፎ የታጀበ፣ ፍትሃዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በቁርጠኝነት እንስራ ብለዋል። በዚህም በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ለመጻኢ እድል ወሳኝ መደላድልን ማመቻቸት አለባችሁ ብለዋል። በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው የወጣቶች ተሳትፎ ተስፋ ሰጪና ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠንካራ መሠረት የጣለ እንደነበር አንስተዋል። በምርጫው ከ150 ሺህ በላይ ወጣቶች በምርጫ አስፈጻሚነትና በታዛቢነት መሰማራታቸውን ገልጸው፤ በዚህም ወጣቶች ለዴሞክራሲያዊ ተቋማት ግንባታ የጀርባ አጥንት መሆን እንደሚችሉ በተግባር አሳይተዋል ብለዋል።   በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይህንን ተሳትፎ ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንደሚገባ ተናግረዋል። ወጣቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያቀርቧቸው ማኒፌስቶዎች ውስጥ የወጣቶች አጀንዳ በትክክል መካተቱን መመርመርና በጥብቅ መከታተል ያስፈልጋል ብለዋል። የወጣቶች በምርጫ መሳተፍ ለስራ እድል ፈጠራ፣ የኢንተርፕራይዞች መስፋፋት፣ የብድር አቅርቦትና የፈጠራ ስራዎች ድጋፍ ምላሽ የሚሰጥ መንግስትና ፖሊሲ ለመምረጥ ያስችላል ሲሉም ተናግረዋል። በንቅናቄው መርሃ ግብር የተሳተፉ ወጣቶችም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ሀላፊነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረው፤ሌሎች ወጣቶችም በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት አባል የሆኑት ወጣት በቃሉ መሰረት እና የምስራች ቶማስ ምርጫ በሀገር ጉዳይ ላይ መወሰን በመሆኑ ወጣቶች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ እስከ ድህረ ምርጫው ባለው ሂደት በንቃት ሊሳተፉ ይገባል ብለዋል።
የክልሉን ሰላም ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Apr 8, 2026 385
ባህር ዳር፤መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በተሰራው የተቀናጀ የህግ ማስከበር ስራ የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፥ የክልሉን ሰላም ለማዝለቅ የተቀናጀ የፀጥታ ማስከበር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ለዚህም የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሎች ከሌሎች የፀጥታ አባላት ጋር በመተባበር የፀጥታ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ባለፉት ጊዜያት በክልሉ የተከሰተው የሰላም እጦት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና መፍጠሩን አንስተው፤መንግስት ችግሩን በመነጋገር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሰፊ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ታጥቀው ጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭን በመቀበል ወደ ሰላማዊ ኑሮ እየመጡ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የክልሉ ህዝብ ሰላምና ልማት አጥብቆ ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ የሰላምን አማራጭ ባልተከተሉ ቡድኖች ላይ የፀጥታ ሃይሉ ህግና ስርዓት የማስከበር ስራውን ህብረተሰቡን ባሳተፈ አግባብ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አክለዋል። የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሉ መጭው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ስጋት መከናወን እንዲችል ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሆነ አስገንዝበዋል። የትንሳኤ በዓልም በሰላም እንዲከበር የተቀናጀ ስምሪት ተሰጥቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመዋል። በበዓል አከባበሩ ወቅት ህብረተሰቡ ማንኛውንም አጠራጣሪ ሁኔታ ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ ሃይል ጥቆማ በመስጠት የሰላሙ ባለቤት መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የዜግነት ክብር መገለጫ ነው
Apr 8, 2026 527
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የዜግነት ክብር መገለጫ መሆኑን አባትና እናት አርበኞች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ሲያካሂድ ቆይቷል። በተጨማሪም ቦርዱ የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሟል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስቻለቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ባህል በመገንባት የሀገር ፍቅርና ክብር የሚገለፅበት የዜጎች የጋራ መድረክ ነው ብለዋል። አባት አርበኛ ባሻ ሽመልስ ወልደ-ተክሌ፤ በኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ካርድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። ዜጎችም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ተጨማሪ የድምፅ መስጫ ካርድ ማውጫ ጊዜን በመጠቀም ካርድ መውሰድ እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄድ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞከራሲ ባህል በመገንባት የዜግነት ክብር መገለጫ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ዜጎች ይበጀናል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት ከወዲሁ በመዘጋጀት ለሀገራቸው ያላቸውን ክብር ማሳየት እንደሚኖርባቸው አንስተዋል።   ሌላኛው አባት አርበኛ ኮሎኔል አያሌው በላይ፤ ምርጫ የዜግነት ክብር መገለጫና ሕገ-መንግስታዊ የመምረጥና መመረጥ መብት ማረጋገጫ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ለመገንባት አንዱ መሳሪያ ነው ያሉት አባት አርበኛ ኮሎኔል አያሌው፤ የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ለማጠናከር የምርጫ ተሳትፎ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል። በዚህም በምርጫ ሂደት ድምፅ ለመስጠት ዕድሜው የሚፈቅድለት ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ በማውጣት ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀት እንዳለበት አስረድተዋል። እናት አርበኛ አልማዝ አንበርብር በበኩላቸው፤ ምርጫ የሀገርን ልማትና ዕድገት ለማስቀጠል ዜጎች በአደባባይ የሚሳተፉበት የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።   ሁሉም ዜጋ ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በማውጣት ለሀገሩ ያለውን ክብር በምርጫ ተሳትፎ ማሳየት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዜጎች የመምረጥና መመረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ይበጀናል ለሚሉት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።  
የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለአምራች ኃይል ግንባታ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 7, 2026 1645
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለአምራች ኃይል ግንባታ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ስኬት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ይህም በተለይ ለጀርባ አጥንት ለሆነው አምራች እና ተመራማሪ ኃይል ግንባታ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አመልክተዋል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በበይነ መረብ ባካሄዱት ውይይት፤ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን፣ የሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የጤና መድህን፣ የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲ እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ የ2018 ዓ.ም የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀምን ገምግመዋል። በዚሁ መድረክ በፌዴራል ደረጃ የተከለሰውን የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ የጸደቀ ሲሆን፣ በእቅዱ የተመለከቱ ቁልፍ ተግባራት በሁሉም የሴክተር መስሪያ ቤቶች እና የክልል ቢሮዎች ተካተው ተግባራዊ እንዲሆኑም መመሪያ ሰጥተዋል። የሰቆጣ ቃል ኪዳን ትግበራን በተመለከተ፣ ኢትዮጵያ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሷን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የ15 ዓመቱ ፍኖተ ካርታ አካል የሆነውን የመጨረሻውን የአምስት ዓመት የማስፋት ምዕራፍ (ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም) የትግበራ እቅድ መጽደቁን ይፋ አድርገዋል። በዚህም የመቀንጨር እና ሌሎች የስርዓተ ምግብ ችግሮችን በፍጥነት ለመቀነስ እስከ አሁን የተገኙ ልምዶችን በመቀመር ማህበረሰቡን በባለቤትነት ማሳተፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። ከዚህ በተጨማሪም የፌዴራል የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ምክር ቤትን ለማቋቋም በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የባለድርሻ አካላት ግብዓት ተካቶበት ወደ ቀጣይ አፈጻጸም እንዲሸጋገር አቅጣጫ ተቀምጧል።   የጤና መድህን አገልግሎትን ይበልጥ ለማጠናከርም በክልል ደረጃ ጠንካራ አስፈጻሚ አካላትን ማደራጀትና በያዝነው ዓመት የፌዴራል ቋት (Pool) መመስረት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ስምምነት ላይ መደረሱንም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት። የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ውጤታማነትን ለማስቀጠልም፣ ዜጎች እንደ መክፈል አቅማቸው መዋጮ የሚያደርጉበት አሰራር መጠናከር እንዳለበትም አመልክተዋል። ፕሮግራሙ ያለው ለሌለው የሚደጋገፍበት ወሳኝ ስርአት በመሆኑም፣ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲ እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ ፍኖተ ካርታን በተመለከተ፣ ቀጣይ የ5 ዓመታት ትግበራዎች በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ እንዲመሩ መወሰኑን ጠቁመዋል። ለዚህም በፌዴራል እና በክልል ደረጃ ለፕሮግራሙ ልዩ ትኩረት በመስጠት በቂ በጀት እንዲመደብና ከተለያዩ ምንጮች የሀብት ማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
አዋጁ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ጉዞን ለማፋጠን ትልቅ ዐቅም ይፈጥራል
Apr 7, 2026 703
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፡- የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አዋጅ የዘርፉን ትራንስፎርሜሽንና ምርታማነት ለማሳደግ ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ "የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ" ላይ የውሳኔ ሐሳብ ካቀረበ በኋላ ምክር ቤቱ መርምሮ አዋጁን ቁጥር 1411/2018 አድርጎ አጽድቋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ የውሳኔ ሐሳቡን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ አዋጁ በመንግሥት ብቻ ተወስኖ የቆየውን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ወደ ባለብዙ ተዋንያን ሥርዓት የሚቀይር ነው። ይህም በዘርፉ የግል ባለሀብቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ሌሎች አካላት በሕጋዊ መንገድ እንዲሳተፉ በር ይከፍታል ብለዋል። አዋጁ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና ዲጂታል አሠራሮችን ለአርሶአደሩ ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም አገልግሎት ሰጪዎች በብቃት ማረጋገጫና በምዝገባ ሥርዓት ውስጥ እንዲያልፉ በማድረግ ፍትሐዊና ጥራት ያለው አገልግሎት ማረጋገጥ ያስችላል ነው ያሉት።   የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፤ አዋጁ ሀገር በቀል ዕውቀትን ከሳይንሳዊ መንገድ ጋር በማዳበር የግብርና ትራንስፎርሜሽኑን ለማሳለጥ ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ እና ጃፓን በፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች ትብብራቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ መከሩ
Apr 8, 2026 11
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጃፓን በፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች ትብብርና አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ መምከራቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ በጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦው ሳዳማና በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ የተመራ የልዑካን ቡድን ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አብዩ እና ከተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮች በተመለከተ የሚደረጉ ትብብሮችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ምክክር ተደርጓል።   ኢትዮጵያና ጃፓን ከዚህ ቀደም በደኅንነትና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ የሚሠሯቸውን ተግባራት በማጠናከር በቀጣናው የሚንቀሳቀሱ ሽብርተኛ ቡድኖችንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል መክረዋል። በሳይበርና በአቪዬሽን ደኅንነት ዙሪያ የሚደረጉትን ትብብሮችና የመረጃ ልውውጦች ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮችም ላይም ተወያይተዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አቢዩ፤ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የተከናወኑ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንዲሁም የፀጥታ ዘርፍ ሪፎርሞችን በተመለከተ ለጃፓን ልዑክ አባላት ገለጻ አድርገዋል። በዚህ ወቅት የሪፎርም ሥራዎቹን ፋይዳም አብራርተዋል፡፡   ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር አሰፋ አቢዩ፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ አማራጭ መንገዶች የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን እንቅስቃሴዎች ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል። የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦው ሳዳማና በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ካላት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እና ተጽዕኖ ፈጣሪነት አኳያ የሁለቱን ሀገራት ትብብርና አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ይሰራል፡፡ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመረጃና በልምድ ልውውጥ እንዲሁም በአቅም ግንባታ መስኮች የተጀመሩ የአጋርነት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን ጥረቶች ጃፓን እንድምትደግፍ ገልፀዋል።   የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት ያደነቁት የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር አማካሪ፤ በአጭር ዓመታት ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ ሪፎርምና ትላልቅ የከተማ ልማት ሥራዎችን መሥራቷ ለሌሎች በአብነት የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያና ጃፓን በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Apr 8, 2026 125
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018(ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያና ጃፓን በጋራ ፍላጎቶቻቸውና በጸጥታ ጉዳይ ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ ኦዌ ሳዳማሳ የተመራውን የልዑካን ቡድን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።   በቆይታቸውም የሁለቱን አገራት ብሄራዊ ጥቅሞች፣ የጋራ ፍላጎትና እሴቶችን ባከበሩ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በቅንጅት መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ዙሪያ ተወያይተዋል። ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካም ሆነ በአህጉር ደረጃ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የምታከናውናቸውን ተግባራት ልዩ አማካሪው ኦዌ ሳዳማሳ አድንቀዋል። በተለይም በሰላም ማስከበር ረገድ ያላትን ሰፊ ተሞክሮ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ጃፓን በዚህ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ያላትን ከፍተኛ ፍላጎት አረጋግጠዋል። ጃፓን የኢትዮጵያን የሰላም ማስከበር ማዕከል አቅም ለመገንባት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የጠቆሙት አማካሪው፤ በስልጠና እና በልምድ ልውውጥ የመከላከያ ሰራዊቱን የሰው ኃይል የሙያ ብቃት ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነትም ገልጸዋል።   ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በበኩላቸው፣ ጃፓን ለትብብር ያሳየችውን ተነሳሽነት በማድነቅ፤ ኢትዮጵያ በእውነተኛ ወዳጅነትና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ወታደራዊ አጋርነትን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አመልክተዋል። ይህ ትብብርም በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ያላቸውን እምነት መግለጻቸውን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያሳያል።
ወጣቶች በምርጫ ላይ በንቃት በመሳተፍ ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ መጎልበት ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው  
Apr 8, 2026 189
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ መጎልበት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባችው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አህመድ ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር "በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የወጣቶች ድምፅና ተሳትፎ ለሠላምና ለዴሞክራሲ“ በሚል መሪ ሀሳብ የወጣቶች ተሳትፎን ለማጎልበት ያለመ የንቅናቄ መርሃ ግብር አካሂዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አህመድ እንደገለጹት፤ ወጣቶች የዲሞክራሲያዊ ስርዓቱ ዋነኛ ምሰሶ በመሆናቸው በምርጫ ሂደቱ ንቁ ተሳታፊ ሊሆኑ ይገባል። በዚህም የሀገሪቱን የልማትና የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ጉዞን ለማፋጠን እንደሚቻል ጠቁመው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በወጣቶች ሙሉ ተሳትፎ የታጀበ፣ ፍትሃዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በቁርጠኝነት እንስራ ብለዋል። በዚህም በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ለመጻኢ እድል ወሳኝ መደላድልን ማመቻቸት አለባችሁ ብለዋል። በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው የወጣቶች ተሳትፎ ተስፋ ሰጪና ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠንካራ መሠረት የጣለ እንደነበር አንስተዋል። በምርጫው ከ150 ሺህ በላይ ወጣቶች በምርጫ አስፈጻሚነትና በታዛቢነት መሰማራታቸውን ገልጸው፤ በዚህም ወጣቶች ለዴሞክራሲያዊ ተቋማት ግንባታ የጀርባ አጥንት መሆን እንደሚችሉ በተግባር አሳይተዋል ብለዋል።   በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይህንን ተሳትፎ ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንደሚገባ ተናግረዋል። ወጣቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያቀርቧቸው ማኒፌስቶዎች ውስጥ የወጣቶች አጀንዳ በትክክል መካተቱን መመርመርና በጥብቅ መከታተል ያስፈልጋል ብለዋል። የወጣቶች በምርጫ መሳተፍ ለስራ እድል ፈጠራ፣ የኢንተርፕራይዞች መስፋፋት፣ የብድር አቅርቦትና የፈጠራ ስራዎች ድጋፍ ምላሽ የሚሰጥ መንግስትና ፖሊሲ ለመምረጥ ያስችላል ሲሉም ተናግረዋል። በንቅናቄው መርሃ ግብር የተሳተፉ ወጣቶችም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ሀላፊነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረው፤ሌሎች ወጣቶችም በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት አባል የሆኑት ወጣት በቃሉ መሰረት እና የምስራች ቶማስ ምርጫ በሀገር ጉዳይ ላይ መወሰን በመሆኑ ወጣቶች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ እስከ ድህረ ምርጫው ባለው ሂደት በንቃት ሊሳተፉ ይገባል ብለዋል።
የክልሉን ሰላም ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Apr 8, 2026 385
ባህር ዳር፤መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በተሰራው የተቀናጀ የህግ ማስከበር ስራ የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፥ የክልሉን ሰላም ለማዝለቅ የተቀናጀ የፀጥታ ማስከበር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ለዚህም የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሎች ከሌሎች የፀጥታ አባላት ጋር በመተባበር የፀጥታ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ባለፉት ጊዜያት በክልሉ የተከሰተው የሰላም እጦት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና መፍጠሩን አንስተው፤መንግስት ችግሩን በመነጋገር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሰፊ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ታጥቀው ጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭን በመቀበል ወደ ሰላማዊ ኑሮ እየመጡ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የክልሉ ህዝብ ሰላምና ልማት አጥብቆ ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ የሰላምን አማራጭ ባልተከተሉ ቡድኖች ላይ የፀጥታ ሃይሉ ህግና ስርዓት የማስከበር ስራውን ህብረተሰቡን ባሳተፈ አግባብ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አክለዋል። የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሉ መጭው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ስጋት መከናወን እንዲችል ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሆነ አስገንዝበዋል። የትንሳኤ በዓልም በሰላም እንዲከበር የተቀናጀ ስምሪት ተሰጥቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመዋል። በበዓል አከባበሩ ወቅት ህብረተሰቡ ማንኛውንም አጠራጣሪ ሁኔታ ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ ሃይል ጥቆማ በመስጠት የሰላሙ ባለቤት መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የዜግነት ክብር መገለጫ ነው
Apr 8, 2026 527
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የዜግነት ክብር መገለጫ መሆኑን አባትና እናት አርበኞች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ሲያካሂድ ቆይቷል። በተጨማሪም ቦርዱ የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሟል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስቻለቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ባህል በመገንባት የሀገር ፍቅርና ክብር የሚገለፅበት የዜጎች የጋራ መድረክ ነው ብለዋል። አባት አርበኛ ባሻ ሽመልስ ወልደ-ተክሌ፤ በኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ካርድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። ዜጎችም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ተጨማሪ የድምፅ መስጫ ካርድ ማውጫ ጊዜን በመጠቀም ካርድ መውሰድ እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄድ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞከራሲ ባህል በመገንባት የዜግነት ክብር መገለጫ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ዜጎች ይበጀናል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት ከወዲሁ በመዘጋጀት ለሀገራቸው ያላቸውን ክብር ማሳየት እንደሚኖርባቸው አንስተዋል።   ሌላኛው አባት አርበኛ ኮሎኔል አያሌው በላይ፤ ምርጫ የዜግነት ክብር መገለጫና ሕገ-መንግስታዊ የመምረጥና መመረጥ መብት ማረጋገጫ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ለመገንባት አንዱ መሳሪያ ነው ያሉት አባት አርበኛ ኮሎኔል አያሌው፤ የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ለማጠናከር የምርጫ ተሳትፎ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል። በዚህም በምርጫ ሂደት ድምፅ ለመስጠት ዕድሜው የሚፈቅድለት ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ በማውጣት ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀት እንዳለበት አስረድተዋል። እናት አርበኛ አልማዝ አንበርብር በበኩላቸው፤ ምርጫ የሀገርን ልማትና ዕድገት ለማስቀጠል ዜጎች በአደባባይ የሚሳተፉበት የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።   ሁሉም ዜጋ ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በማውጣት ለሀገሩ ያለውን ክብር በምርጫ ተሳትፎ ማሳየት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዜጎች የመምረጥና መመረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ይበጀናል ለሚሉት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።  
የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለአምራች ኃይል ግንባታ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 7, 2026 1645
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለአምራች ኃይል ግንባታ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ስኬት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ይህም በተለይ ለጀርባ አጥንት ለሆነው አምራች እና ተመራማሪ ኃይል ግንባታ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አመልክተዋል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በበይነ መረብ ባካሄዱት ውይይት፤ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን፣ የሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የጤና መድህን፣ የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲ እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ የ2018 ዓ.ም የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀምን ገምግመዋል። በዚሁ መድረክ በፌዴራል ደረጃ የተከለሰውን የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ የጸደቀ ሲሆን፣ በእቅዱ የተመለከቱ ቁልፍ ተግባራት በሁሉም የሴክተር መስሪያ ቤቶች እና የክልል ቢሮዎች ተካተው ተግባራዊ እንዲሆኑም መመሪያ ሰጥተዋል። የሰቆጣ ቃል ኪዳን ትግበራን በተመለከተ፣ ኢትዮጵያ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሷን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የ15 ዓመቱ ፍኖተ ካርታ አካል የሆነውን የመጨረሻውን የአምስት ዓመት የማስፋት ምዕራፍ (ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም) የትግበራ እቅድ መጽደቁን ይፋ አድርገዋል። በዚህም የመቀንጨር እና ሌሎች የስርዓተ ምግብ ችግሮችን በፍጥነት ለመቀነስ እስከ አሁን የተገኙ ልምዶችን በመቀመር ማህበረሰቡን በባለቤትነት ማሳተፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። ከዚህ በተጨማሪም የፌዴራል የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ምክር ቤትን ለማቋቋም በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የባለድርሻ አካላት ግብዓት ተካቶበት ወደ ቀጣይ አፈጻጸም እንዲሸጋገር አቅጣጫ ተቀምጧል።   የጤና መድህን አገልግሎትን ይበልጥ ለማጠናከርም በክልል ደረጃ ጠንካራ አስፈጻሚ አካላትን ማደራጀትና በያዝነው ዓመት የፌዴራል ቋት (Pool) መመስረት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ስምምነት ላይ መደረሱንም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት። የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ውጤታማነትን ለማስቀጠልም፣ ዜጎች እንደ መክፈል አቅማቸው መዋጮ የሚያደርጉበት አሰራር መጠናከር እንዳለበትም አመልክተዋል። ፕሮግራሙ ያለው ለሌለው የሚደጋገፍበት ወሳኝ ስርአት በመሆኑም፣ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲ እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ ፍኖተ ካርታን በተመለከተ፣ ቀጣይ የ5 ዓመታት ትግበራዎች በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ እንዲመሩ መወሰኑን ጠቁመዋል። ለዚህም በፌዴራል እና በክልል ደረጃ ለፕሮግራሙ ልዩ ትኩረት በመስጠት በቂ በጀት እንዲመደብና ከተለያዩ ምንጮች የሀብት ማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
አዋጁ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ጉዞን ለማፋጠን ትልቅ ዐቅም ይፈጥራል
Apr 7, 2026 703
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፡- የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አዋጅ የዘርፉን ትራንስፎርሜሽንና ምርታማነት ለማሳደግ ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ "የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ" ላይ የውሳኔ ሐሳብ ካቀረበ በኋላ ምክር ቤቱ መርምሮ አዋጁን ቁጥር 1411/2018 አድርጎ አጽድቋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ የውሳኔ ሐሳቡን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ አዋጁ በመንግሥት ብቻ ተወስኖ የቆየውን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ወደ ባለብዙ ተዋንያን ሥርዓት የሚቀይር ነው። ይህም በዘርፉ የግል ባለሀብቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ሌሎች አካላት በሕጋዊ መንገድ እንዲሳተፉ በር ይከፍታል ብለዋል። አዋጁ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና ዲጂታል አሠራሮችን ለአርሶአደሩ ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም አገልግሎት ሰጪዎች በብቃት ማረጋገጫና በምዝገባ ሥርዓት ውስጥ እንዲያልፉ በማድረግ ፍትሐዊና ጥራት ያለው አገልግሎት ማረጋገጥ ያስችላል ነው ያሉት።   የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፤ አዋጁ ሀገር በቀል ዕውቀትን ከሳይንሳዊ መንገድ ጋር በማዳበር የግብርና ትራንስፎርሜሽኑን ለማሳለጥ ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ማህበራዊ
የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በባህር ዳር ከተማ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ የማጋራት ተግባር ተከናወነ 
Apr 8, 2026 57
ባህር ዳር ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ በባህር ዳር ከተማ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መርሀግብር ተከናወነ። የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሰብለ ዘውዱ በማዕድ ማጋራት መርሀግብሩ ላይ እንደገለጹት፣ በዓልን በመደጋገፍ በአብሮነት የማሳለፍ እሴት ተጠናክሮ ቀጥሏል።   በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የተለያዩ አካላትን በማስተባበር አቅመ ደካማ ወገኖች በዓልን ተደስተው እንዲያሳልፉ የተጀመረው የድጋፍ ሥራ ውጤት እየታየበት መሆኑን ተናግረዋል። በዛሬው እለትም ለ400 አቅመ ደካሞች የበዓል መዋያ ድጋፍ መደረጉን ገልጸው፣ በዚህም ለእያንዳንዳቸው የዳቦ ዱቄት፣ የዘይት እና የዶሮ ድጋፍ ተደርጓል ብለዋል። መምሪያው ባለድርሻ እና አጋር አካላትን በማስተባበር ከሚያደርገው ከዕለታዊ ድጋፍ በተጨማሪ ለዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ወይዘሮ ሰብለ አስረድተዋል። ከድጋፉ ተጠቃሚዎች መካከል ወይዘሮ እናት በሽር በሰጡት አስተያየት የተደረገላቸው ድጋፍ በዓሉን ያለሀሳብ ከቤተሰባቸው ጋር ተደስተው ለማሳለፍ እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።   ድጋፍ ላደረጉላቸው አካላት ምስጋናቸውን ያቀረቡት ወይዘሮዋ፣ ድጋፉ ተጠናክሮ ሌሎችም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጠይቀዋል። አቶ አስማረ አያሌው የተባሉ ሌላው የማዕድ ማጋራቱ ተጠቃሚ በበኩላቸው በአቅም ማነስ ለበዓል እየተጨነቁ ባለበት ወቅት የድጋፉ ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውን ነው የገለጹት። በዛሬው እለት የተደረገላቸው የበዓል መዋያ ድጋፍ በዓሉን ከቤተሰባቸው ጋር በአብሮነትና በደስታ ለማሳለፍ እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ አጋሩ 
Apr 8, 2026 108
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አከናውነዋል። ፕሬዝዳንቱ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ማዕድ ማጋራት በፈጣሪ ዘንድ የተወደደ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቅመ ደካማ ወገኖች በበዓላት ወቅት በራቸውን ዘግተው ማሳለፍ የለባቸውም በሚል የጀመሩት ተነሳሽነት ኢትዮጵያዊ የመረዳዳት ባህል ይበልጥ እንዲዳብር ማድረጉን ጠቅሰዋል። ይህ የመረዳዳት ተግባር በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች በበዓል ወቅት ቤታቸው ባዶ እንዳይሆንና ከሌላው ወገኖች ጋር በጋራ እንዲያሳልፉ የሚያስችል መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።   የመንግስት ዋነኛ ዓላማ ሁሉም ዜጋ ራሱን ችሎ የተሻለ ህይወት እንዲመራ ማስቻል መሆኑን ያመለከቱት ፕሬዝዳንቱ፤ ለዚህም መንግስት በሰው ተኮር ፖሊሲው በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ሰባተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ይካሄዳል
Apr 8, 2026 138
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ሰባተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስን በሚመለከት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኮንፍረንሱ ከሚያዚያ 7 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ጠቁመዋል፡፡ በኮንፍረንሱ ላይ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምን ለማፅናት በሚያስችሉና በሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት የፓናል ውይይት እና ህዝባዊ ውይይት እንደሚካሄድ ገልጸዋል። ከኮንፍረንሱ በተጨማሪ በክልሉ ያሉ የልማት ስራዎች ጉብኝት፣ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብርና ሌሎች የተለያዩ ሁነቶች እንደሚከናወኑ አብራርተዋል። ለሁለት ቀናት በሚኖረው ኮንፍረንስ ላይ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የሃይማኖት አባቶች፣ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚሳተፉም አክለዋል። ጉባኤው ከዚህ ቀደም በተለያዩ ክልሎች ባካሄዳቸው ስድስት የሰላም ኮንፍረንሶች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ አዎንታዊ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። የሃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ለዜጎች የሰላም ጥሪን በማስተላለፍና በማስተማር ለሰላም ዘብ የሆነ ትውልድን ለመፍጠር ትልቅ ሚና መጫወት ችለዋል ብለዋል። ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችም ለስሙነ ህማማት እና ለስቅለት በአል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ህብረተሰቡ የትንሳኤ በዓልን ሲያከብር  የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ ሊሆን ይገባል
Apr 8, 2026 61
ጎንደር ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ ህብረተሰቡ የትንሳኤ በዓልን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍና የአብሮነት እሴቱን በማስቀጠል ሊሆን እንደሚገባ ተመላከተ። በዓላት የህብረተሰቡ የመረዳዳት ባህል የሚታይባቸውና በመደጋገፉ ውስጥ የነበሩ የአብሮነት እሴቶች የሚገለጹባቸው ናቸው። ይህንንም ከግምት ባስገባ መልኩ በጎንደር ከተማ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ተካሄዷል።   የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ ደብሬ የኋላ፣ በማዕድ ማጋራት ስነ ስርዓቱ ላይ በመገኘት እንደገለጹት በዓላት ሲመጡ የተቸገሩና አቅመ ደካማ ወገኖችን ማሰብ የዜግነት ግዴታ ነው።   የትንሳኤ በዓልን ምእመኑ ሲያከብርም ያለው ለሌለው በማካፈልና የአብሮነት እሴቱን በሚያጠናክር መልኩ በጋራ በዓሉን በማሳለፍ መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። በከተማ አስተዳደሩ ገንዘብ መምሪያ የፕሮጀክት ክትትልና የበይነ መንግስታት አስተባባሪ አቶ አበበ ካሴ በበኩላቸው፤ ከማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለ200 አቅመ ደካማ ወገኖች የማእድ ማጋራት መርሃ ግብር ተከናውኗል ብለዋል።   በዚህም በከተማው ከሚንቀሳቀሱ 29 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በተገኘ 600 ሺህ ብር ለበዓል መዋያ የምግብ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ለእያንዳንዳቸው አንድ አንድ ሺህ ብር መስጠት መቻሉን ተናግረዋል፡፡   ከድጋፉ ተጠቃሚዎች መካከል እማሆይ እንይሽ ሽፈራው ለተደረላቸው ድጋፍ አመስግነው በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የአብሮነት እንዲሆን ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡   ሌላዋ የድጋፉ ተጠቃሚ ወይዘሮ ፍርዴ አስቻለው በበኩላቸው የተደረገልኝ ድጋፍ በዓሉን ከልጆቼ ጋር በደስታ እንዳሳልፍ እድል የፈጠረልኝ በመሆኑ ምስጋናዬ ወደር የለውም ብለዋል፡፡
ኢኮኖሚ
በገንዳውኃ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ የተከማቸ ከ950 ሊትር በላይ ነዳጅ ተያዘ
Apr 8, 2026 16
ገንዳውኃ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳውኃ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረ ከ950 ሊትር በላይ ነዳጅ መያዙን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ሀይሌ ብርሃኑ 900 ሊትር ናፍጣ እና 56 ሊትር ቤንዚን በግለሰብ ቤት ከተደበቀበት ለመያዝ መቻሉን ገልጸዋል።   በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረው ነዳጅ ሊያዝ የቻለው የጸጥታ አካላት ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻና ጥብቅ ክትትል መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ ነዳጁ በህገወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘው በከተማው ቀበሌ 03 ልዩ ቦታው ቀጠና 08 በተባለ አካባቢ ነው።   በቀጣይም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጫና የሚፈጥሩ መሰል ህገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የቁጥጥር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ህብረተሰቡ ህገ ወጥ ተግባር ተፈጽሞ ሲያይ ለጸጥታ አካላት ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለውን ትብብር በቀጣይም አጠናክሮ እንዲቀጥል ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።
የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው
Apr 8, 2026 63
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። ቋሚ ኮሚቴው በጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ የአስረጂ መድረክ አካሂዷል። በዚሁ ወቅት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ፤ በረቂቅ አዋጁ ሥርዓት ክፍተትን የሚያርሙ ድንጋጌዎች እንደተካተቱ ገልጸዋል።   የኢትዮጵያን አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የንግድ ተወዳዳሪነትን የሚያሳልጥ ዓለም አቀፍና አዳዲስ የጉምሩክ አገልግሎት ማቀላጠፊያ ድንጋጌዎች መካተታቸውን ተናግረዋል። በዚህም የአዋጁ ማሻሻያ የኮሚሽኑን ተግባርና ኃላፊነት በተቀላጠፈ የአሰራር ሥርዓት በመምራት ውስብስብ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን መግታት በሚያስችል መልኩ እየተዘጋጀ ነው ብለዋል። የምክር ቤቱ አባላትና የሕግ ሙያተኞችም፤ በረቂቅ አዋጅ ላይ ምላሽና ማብራሪያ የሚሹ ጉዳዮችን በማስመልከት ለሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች አስተያየትና ጥያቄ አቅርበዋል። በረቀቂ አዋጁ ላይ የገቢ ምርቶችን የቆይታ ጊዜ በማስመልከት ከዚህ ቀደም ከነበረው አንፃር ሲታይ ከፍ እንዲል መደረጉን በማስመልከት ምላሽና ማብራሪያ ጠይቀዋል።   የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በምላሽና ማብራሪያቸው፤ የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ከዚህ ቀደም የነበሩ የአሰራር ክፍተቶችን ለማረም ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በዚህም በረቂቅ አዋጁ ውስብስብ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን መከላከል የሚያስችሉ ወሳኝ ድንጋጌዎችን በማካተት እየተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። የጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ የኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የሚያቀላጥፍ አስቻይ የጉምሩክ አገልግሎት አሰጣጥ ተቋማዊ የሪፎርም አካል መሆኑን ገልጸዋል።   በተጨማሪም በዕቃዎች የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት የሚጠናቀቅበት ጊዜ፣ የዋጋ አወሳሰን፣ በይግባኝ አቀራረብ፣ በጉምሩክ ጥሰት የሚወረሱ ንብረቶች አስተዳደር፣ የዋስትና አያያዝ ላይ የተደረጉ ጉልህ ማሻሻያዎች ላይም ማብራርያ ሰጥተዋል። በገንዘብ ሚኒስቴር የታክስ ጉዳዮች አማካሪ ዋሲሁን አባተ፤ በረቀቂ አዋጁ ላይ የጉምሩክ ሥነ-ስርዓትን ያሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ወሳኝ ድንጋጌዎች መካተታቸውን አስረድተዋል። በዚህም በረቂቅ አዋጁ ላይ የጉምሩክ አገልግሎቶችን የሚያቀላጥፉ አመቺና አዳዲስ ዓለም አቀፍ የአሰራር ሥርዓት መርሆችና ድንጋጌዎች እንደተካተቱ አስገንዝበዋል።
በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል
Apr 8, 2026 68
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡ በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ መንግስቱ ሂርባዬ በዞኑ በበልግ አዝመራ 294 ሺህ 389 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ዕቅድ ተይዟል ብለዋል። እስካሁን በተካሄደው ስራም 260 ሺህ 780 ሄክታር መሬት በአራት ዋና ዋና ሰብሎች በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል፡፡   የተጠቀሰው ሄክታር መሬትም በበቆሎ፣ በስንዴ፣ በጤፍ፣ በቦሎቄና በሌሎች ሰብል ዘር መሸፈኑን ገልጸው የግብርና ስራውን ለማሳካትም የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦቱም በወቅቱ ለአርሶ አደሩ መድረሱን ጠቁመዋል። በዘር ከተሸፈነው መሬትም እስካሁን 239 ሺህ 230 ሄክታር በመስመር፣ 175 ሺህ 209 ሄክታሩ ደግሞ በኩታ ገጠም የእርሻ ስነ-ዘዴ መልማቱን አስታውቀዋል፡፡ በዞኑ ቆላማ አካባቢ የዝናቡ ስርጭት የሚቆየው ለተወሰነ ጊዜ በመሆኑ የዘር ስራውን ለማፋጠን በርካታ ትራክተሮች መሰማራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በበልግ አዝመራ ልማቱ ከ95 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች መሳተፋቸውን ተናግረዋል፡፡ ምርታማነቱን ለማሳደግም ከ95 ሺህ 403 ኩንታል በላይ ማዳበሪያና 42 ሺህ 262 ኩንታል የምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ መከፋፈሉንም አብራርተዋል፡፡ በዞኑ በበልግ አዝመራ ከሚለማው መሬትም ከ7 ሚሊዮን 175 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል፡፡   በዞኑ አዶላ ወረዳ የሞኤ ቦኮ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሹና ጎበና ለበልግ አዝመራ ያዘጋጁትን መሬት በዘር በመሸፈን ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ምርታማነታቸውንም ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያ ምርጥ ዘር መጠቀማቸውን ተናግረዋል፡፡ በዞኑ ያለው ደጋ፣ ወይና ደጋና ቆላማ የአየር ጸባይ ለሰብል ልማትና ለእንስሳት እርባታ አመቺ መሆኑ ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ በ2040 ዓመታዊ ገቢውን 30 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ አቅዷል
Apr 8, 2026 125
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ በ2040 ዓመታዊ ገቢውን 30 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ማቀዱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለፁ። አየር መንገዱ ፈተናዎችን በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡንም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የአየር መንገዱ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው፤ ተቋሙ ባለፋት ስምንት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያ የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን ገልጸዋል። አየር መንገዱ የመጀመሪያ በረራውን መጋቢት 30 ቀን 1938 ዓ.ም ማድረጉን ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በነበሩት ዓመታት ባስመዘገበው ተከታታይ ዕድገት በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ 145 መዳረሻዎች ያሉት ግዙፍ አየር መንገድ ለመሆን መብቃቱን ተናግረዋል። ተቋሙ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተወዳዳሪነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ራዕይ 2040 የተሰኘ ስትራቴጂክ እቅድ ማዘጋጀቱን አስታውቀዋል። ይህ እቅድ አየር መንገዱ በሚቀጥሉት ዓመታት የበረራ አድማሱን፣ የንብረት አቅሙን እና የገቢ መጠኑን በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ የሚያስችለው ነው ብለዋል። በዚህም መሰረት አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት ያሉትን 145 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን ወደ 243 ለማድረስ ማቀዱን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት አገልግሎት እየሰጡ ያሉትን 150 አውሮፕላኖች ከእጥፍ በላይ በማሳደግ ቁጥራቸውን 350 ለማድረስ ታቅዷል ነው ያሉት። ዓመታዊ መንገደኞችን የማጓጓዝ አቅሙን አሁን ካለበት 20 ሚሊዮን ወደ 60 ሚሊዮን ከፍ ለማድረግ ግብ መቀመጡንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በዓመት የሚጓጓዘውን 850 ሺህ ቶን የጭነት መጠን ወደ 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ቶን ለማሳደግ ታቅዷል ነው ያሉት። አየር መንገዱ በስትራቴጂክ እቅዱ ዓመታዊ ገቢውን 30 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ግብ መያዙን ዋና ስራ አስፈፃሚው አስታውቀዋል። የአሁኑ የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የታቀደውን ግዙፍ ዕድገት ለማስተናገድ በቂ ባለመሆኑ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፈያ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። ከዓለም አቀፍ በተጨማሪ የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎችን በእጥፍ ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የዲጅታል ልማት ስትራቴጂ ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት ነው
Apr 8, 2026 97
መቀሌ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የዲጅታል ልማት ስትራቴጂ ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትግበራ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በቀጣይ አምስት ዓመታት የሚከናወን ቀጣይነት ያለው ስትራቴጂክ ፕላን ይፋ በማድረግ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል። የ2025 ስትራቴጂክ ተግበራ ስኬት ተደርገው ከሚወሰዱት መካከል የባንኮች የዲጅታል አገልግሎት መሳለጥ፣ የቴሌብር አገልግሎት፣ የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ፣ የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና እና ሌሎችም ይገኙበታል። የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ፤ የአዳዲስ ፈጠራዎች፣ የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ በዲጅታል የታገዙ መሆናቸውም ለዘርፉ እድገትና ማንሰራራት ማሳያዎች መሆናቸውን መግለጽ ይቻላል። ከዚህ ስኬትም በመነሳት የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ይፋ ተደርጎ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ይገኛል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ በትግራይ ክልል ያነጋገራቸው የዘርፉ ባለሙያዎች በዲጅታል ልማት ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራት አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከባለሙያዎቹ መካከል ሰሎሞን ፀጋይ፤ በተለይም የቴሌብር አገልግሎት፣ የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ፣ የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና ለዘርፉ መሰረት ያኖሩ መሆናቸውን አስረድተዋል። የተቋማት የዲጅታል አገልግሎት እየተስፋፋ መምጣት ሌላኛው ስኬት መሆኑንም ጠቅሰዋል። ከዚህ ስኬት በመነሳትም በቀጣይ አምስት አመታት የሚተገበረው ስትራቴጂክ እቅድ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑን ገልጸዋል። የድጅታል ቴክኖሎጂ ምርምርና ጥናት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሰሎሞን ገብረመድህን በበኩላቸው በተለይም ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው ለዘርፉ ልማትና አድገት ትልቅ አቅም መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እቅድን ለማሳከት ስልጠናዎች እንዳሉ ሆነው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የዘርፉ ባለሙያዎች በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ሌላኛው የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሀጎስ ገብረፃድቅ፤ በዲጅታል ቴክኖሎጂ እንደ ሀገር የተከናወኑ ተግባራትና በቀጣይ የተያዙ እቅዶች የሚያጓጉ መሆኑን ገልጸዋል። በገጠርና በከተሞች የዲጅታል አገልገግሎትን በማስፋት ዜጎች ፈጣን፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ መትጋት ይጠበቅብናል ብለዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከልም የዲጅታል ትግበራ የማይተካ ሚና የሚኖረው መሆኑን አስረድተዋል።  
የአርማወር ሐንሰን ምርምር ኢንስቲትዩት ችግር ፈቺ የምርምርና ፈጠራ ውጤቶችን እያበረከተ ነው
Apr 7, 2026 191
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በሳይንሳዊ ምርምርና በፈጠራ ሥራዎች በሀገርና በአህጉር ደረጃ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጡ ውጤቶችን እያስመዘገበ መሆኑን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም የተገነባውንና ዘመናዊ መሠረተ ልማቶችን የያዘውን የምርምር ማዕከል መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መርቀው ከፍተዋል።   በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክትም ማዕከሉ ኢትዮጵያና አፍሪካ በሳይንሱ ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲሸጋገሩ ትልቅ መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል። ይህ ዘመናዊ የምርምር ማዕከል ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ በመድሃኒትና በክትባት ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ሥፍራ መሆኑን ተናግረዋል። የአርማወር ሐንሰን ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በከፍተኛ አቅምና በውጤታማነት እየሠራ ነው። ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለይም እንደ ሳንባ ነቀርሳ (ቲቢ)፣ ወባ፣ ሚኒንጃይትስና ኒሞኒያ ባሉ ተላላፊ በሽታዎች ላይ ውጤታማ ጥናቶችን ማድረጉን ጠቅሰዋል። ለአብነትም የሳንባ ነቀርሳ ሕክምና ጊዜን ለማሳጠር የተደረገው ምርምር ለሕዝቡ የጤና ችግር ቀጥተኛ መፍትሔ የሚሰጥ ነው ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ በዓለም አቀፍ የሳይንስ መድረክ ላይ የኢትዮጵያን አሻራ በጉልህ እያሳረፈ መሆኑንም ጠቅሰዋል።   በየዓመቱ ከ80 እስከ 100 የሚደርሱ የምርምር ሥራዎች በታዋቂ የሳይንስ መጽሔቶች ላይ እንዲታተሙ በማድረግ ኢትዮጵያንና አፍሪካን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በስፋት እያስተዋወቀ ነውም ብለዋል። የተጠናቀቁና ውጤታማነታቸው የተረጋገጠ ምርምሮችም በቅርቡ ለሕዝብ ይፋ እንደሚሆኑ ፕሮፌሰር አፈወርቅ አረጋግጠዋል። ትኩረቱን ይበልጥ በማስፋት ከተላላፊ በሽታዎች በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት በስፋት እየታዩ ባሉ ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ላይ ጥናቶችን እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ ከጤና ዘርፍ ባለፈ ከሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የተለያዩ የሕክምና መሣሪያዎችን በማምረት ላይ እንደሚገኝም አንስተዋል።
ዩኒቨርሲቲው የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቷል
Apr 4, 2026 291
ወላይታ ሶዶ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። በዩኒቨርሲቲው "የአፈር ለምነትንና ጤናማነትን ማስጠበቅ ለግብርና ሽግግር" በሚል መሪ ሃሳብ 14ኛው ዙር ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ተካሂዷል። በወቅቱ በዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አክበር ጩፎ(ዶ/ር) እንደገለፁት፤ ዩኒቨርሲቲው የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል። የአፈር ለምነትና ጤናማነትን መጠበቅ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድግ በመሆኑ ለግብርና ዘርፍ ምርምሮች ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን በዘርፉ የተሰማሩ ተመራማሪዎችን በመደገፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡   ዩኒቨርሲቲው በበጀት ዓመቱ ከ79 ሚሊየን ብር በላይ በጀት በመመደብ ከ50 በላይ የምርምር፣ 54 የማህበረሰብ ተኮር እንዲሁም ከ14 በላይ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን እየሰራ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ(ዶ/ር) ናቸው። በዩኒቨርሲቲው ያለውን ዕውቀት ከሀብት ጋር ለማቀናጀት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ስለመሆኑም ገልጸዋል። በዚህም የዘንድሮው 14ኛው ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ የአፈር ጤንነትና ምርታማነት ላይ አተኩሮ መዘጋጀቱን ጠቁመው በዘርፉ የተሰማሩ ምሁራንና ባለሙያዎች ቅንጅታቸውን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል አበክረው መስራት እንዳለባቸውም አመልክተዋል።   በዩኒቨርሲቲው የአፈር ሳይንስ ጥናት ፕሮፌሰር ፋኑኤል ላዕከማርያም ፅሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት በአፈር ዙሪያ የሚደረጉ ምርምሮች ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር የሰው፣ የአካባቢ እና የእንስሳትን ጤና ለማስጠበቅ ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ። በጥናታዊ ጽሁፋቸው የአፈር እርጥበትን ማስጠበቅ፣ አሲዳማነትን መቀነስ፣ ምርታማነትን መጨመርና ካርቦንን አምቆ የመያዝ አቅምን ማሳደግ ላይ ያተኮረ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም የተለያዩ ጥናቶች መስራታቸውን ጠቁመው ይህም መንግስት ዘርፉን ለማሻሻል የጀመረውን ውጥን የሚደግፍ በመሆኑ ወደ አርሶ አደሮች በማምጣት እንደሚተገበርም አስረድተዋል።   በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የተፈጥሮ ሀብት አያያዝና የአየር ንብረጥ ለውጥ መቋቋም ፕሮግራም ዳይሬክተር አወቀ ሙሉዓለም(ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋማቸው የሀገሪቱን ግብርና ለማሻገር በጥናት የተደገፈ ስራ በመስራት የግብርናን ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ መንግስት በዘርፉ የያዘውን ውጥን ለማሳካት እየተጋ መሆኑን በመጥቀስ ለስራው ውጤታማነት ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ይህም አርሶ አደሩ ከቤተሰብ ፍጆታ ያለፈ ትርፍ ምርት በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ገበያን በማረጋጋት በኩል አበርክቶ እንዲኖረው ትልቅ ድርሻ መወጣቱን አመልክተዋል። በመድረኩ ከ10 በላይ ጥናታዊ ጽሁፎች የቀረቡ ሲሆን ሙያዊ ውይይት ተደርጎ የፖሊሲ አቅጣጫ የማመላከት ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል።
በምርምር ስራዎች የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገው ጥረት ይጠናከራል
Apr 4, 2026 514
ሰመራ፣መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ) ፡-በምርምር ስራዎች የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት ማጠናከር እንደሚገባ የሠመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ዓሊ ተናገሩ። በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠነኛ ጊዜ የተዘጋጀ የአደጋ ተጋላጭ ማህበረሰብ ዝግጁነትና መቋቋም ላይ ያተኮረ ሲምፖዚየም በሰመራ ከተማ ተካሄዷል።   በመድረኩ ላይ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እንደተናገሩት፤ የምርምር ስራዎችን በማጠናከርና ተግባራዊ በማድረግ የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት መደገፍ ይገባል። የምርምር ውጤቶቹ ማህበረሰቡን ከማንቃትና ተጋላጭ እንዳይሆኑ ከማድረግ አኳያ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። በተለይም ተመራማሪዎች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት የአካባቢውን ችግር ተረድተው እገዛ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተው በአካባቢው የሚገነቡ ህንፃዎች ጭምር ግምት ውስጥ ሊገቡ እንደሚገባም አመልክተዋል። በሲምፖዚየሙ ላይ የተገኙት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመሬት መንቀጥቀጥ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አታላይ አየለ በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ አደጋዎች ከመከሰታቸው በፊት ዝግጅት ማድረጉ የጉዳት መጠኑን ለመቀነስ እገዛ ያደርጋል ብለዋል።   የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ውሳኔ ሰጪ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ማድረግ፣ ፖሊሲዎችን ማጤንና የህንፃ ግንባታ ደረጃ ግልፅ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። መገናኛ ብዙሃን ጉዳዩን አስመልክተው እያከናወኑ ያለው የግንዛቤ ማስጨበጥ ተግባር ሊጠናከር እንደሚገባ ጠቁመው የምርምር ግኝቶችን በየጊዜው በማውጣት ለሚመለከታቸው አካላት ማጋራት ይገባል ብለዋል። በመድረኩም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተመራማሪዎች፣ የትምህርት ሚኒስቴርና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።  
ስፖርት
ኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ከሞሮኮ፣ ቱኒዚያ እና ግብጽ ጋር ተደለደለች
Apr 8, 2026 50
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ድልድል ዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ዛሬ በግብጽ ካይሮ ተካሄዷል። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጇ ሞሮኮ፣ቱኒዚያ እና ግብጽ ጋር ተደልድላለች። በአሜሪካው አሰልጣኝ ቤንጃሚን ዚመር የሚመራው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ለውድድሩ በአዲስ አበባ ዝግጅቱን እያደረገ ይገኛል። በዕጣው መሰረት በምድብ ሁለት ኮትዲቯር፣ ካሜሮን፣ ዩጋንዳ እና ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ተደልድለዋል። ማሊ፣ አንጎላ፣ ታንዛንያ እና ሞዛምቢክ በምድብ ሶስት የሚገኙ ሀገራት ናቸው። ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ አልጄሪያ እና ጋና የሚገኙበት ምድብ አራት ጠንካራው ምድብ ነው። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በሕዳር ወር 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ሶስተኛ መውጣቱን ተከትሎ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ የሚታወስ ነው። 16ኛው የአፍሪካ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ከሚያዚያ 17 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ 16 ሀገራት ይሳተፋሉ። በአፍሪካ ዋንጫው ከሚሳተፉ 16 ሀገራት መካከል የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ 10 ሀገራት በጥቅምት እና ህዳር ወር 2019 ዓ.ም በኳታር ለሚካሄደው 20ኛው የፊፋ ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ያልፋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ለአፍሪካ ምሳሌ ናቸው
Apr 8, 2026 123
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ፣ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከልና ምላሽ ለአፍሪካውያን ምሳሌ የሆኑ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት 16ኛው የአፍሪካ አደጋ ሥጋት አቅም አህጉራዊ ጉባኤ "ለሉዓላዊነት መተባበር" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን እየተካሄደ ነው።   39 የአፍሪካ አደጋ ሥጋት አቅም አባል ሀገራትና ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን እየተሳተፉበት የሚገኘው ይህ ጉባኤ፤ በአፍሪካውያን መካከል ትብብርና አጋርነትን በመፍጠር አህጉራዊ የአደጋ ሥጋትን የመከላከልና የፋይናንስ አቅምን ማጠናከርን ያለመ ነው። የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካውያን የምግብ ሉዓላዊነትን በራሳቸው አቅም ለማረጋገጥ ለጋራ ግብ የሚተባበሩበት ወሳኝ ወቅት ላይ ናቸው፡፡ የአፍሪካ የአደጋ ሥጋት አቅም አህጉራዊ የምግብ ሉዓላዊነትን በራስ አቅም ለማሳካት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ የተቀናጀ የአደጋ ሥጋት ምላሽ መስጠት የሚያስችል አህጉራዊ የፋይናንስ አቅም መገንባት ይገባል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ግቦችን በማሳካት የምንመኛትን አፍሪካ ለመገንባት የሀገራት ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነትና ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ስርዓት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ቀዳሚ አጀንዳ መደረጉን ገልጸው፤ ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠር የተሟላ ድጋፍ ማድረግ የሚያስችል አቅም ተገንብቷል ብለዋል፡፡   ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ አረንጓዴ አሻራ፣ መስኖ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የታዳሽ ኃይል እና ሌሎችም ኢንሼቲቮች የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን በመከላከል እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን በመመከት፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥና የአደጋ ምላሽ በመስጠት ለአፍሪካና ለዓለም ምሳሌ እየሆነች ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ያሳየችው ስኬት ጉባኤውን ለማስተናገድ ተመራጭ እንዳደረጋትም ኮሚሽነሩ አንስተዋል። የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም ጉባኤ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም በማሟላትና የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ያስመዘገበቻቸውን ተሞክሮዎች የምታጋራበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ሥርዓት ለመገንባት የተገበረቻቸው ኢኒሼቲቮች የምግብ ሉዓላዊነትን እና የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማሳካት እንደሚያስችሉ ተናግረዋል፡፡ በአዲስ አበባ የሚሰሩ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን መከላከልና የአደጋ ምላሽ በመስጠት ለአፍሪካውያን ምሳሌ የሆኑ የተግባር ማሳያዎች ናቸው ብለዋል፡፡
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ ነው
Apr 8, 2026 98
አሶሳ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ ዑራ ወረዳ የችግኝ ጣቢያዎች በመገኘት ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ ዝግጅትን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።   ከጉብኝቱ በኋላ ባደረጉት ንግግርም በክልሉ ብሎም እንደ ሀገር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የልማት ስራው ዘንድሮም ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አንስተው ለዚህም በክልሉ በቂ የችግኝ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።   ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን በጉብኝታችን አረጋግጠናል ብለዋል። ከዚህ ፊት የተተከሉ ችግኞች ያሉበትን ደረጃ እና በወረዳው በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችንም ርእሰ መስተዳድሩ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ከካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ የደን አያያዝ ስራዎችን እያከናወነች ነው
Apr 4, 2026 188
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ ዘላቂ የመሬትና የደን አስተዳደር ልምዶችን እያሳደገች መሆኑን የአረንጓዴ አሻራ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) ገለጹ። ዶክተር አደፍርስ ወርቁ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የካርበን ክምችት መኖሩን በማንሳት፤ አብላጫው በደን ሀብት ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ ሀገሪቱ ከካርበን ሽያጭ የምታገኘው ገቢ እንዲጨምር የጎላ ሚና እየተጫዎተ እንዳለ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ የብዝሃ ህይወት ባለቤት በመሆኗ የተሻለ የካርበን ክምችት ለመያዝ የሚያስችል ተስማሚ ሥነ-ምህዳር እንዳላት ዶክተር አደፍርስ ገልጸዋል። ሀገሪቱ በአየር ንብረትና በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈች መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ካርበንን ከአየር ላይ በማስወገድ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ መንገድ እንዲከማች እያደረገ ነው ብለዋል። ቀደም ሲል በደን መመንጠርና ባልተገባ የመሬት አያያዝ ምክንያት ወደ ህዋ ይለቀቅ የነበረውን ሙቀት አማቂ ጋዝ መከላከል የሚያስችሉ ተግባራት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካይነት እየተተገበሩ እንዳለ አስረድተዋል። በዚህም ከካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ ዘላቂ የመሬት እና የደን አሥተዳደር ልምዶችን ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልጸዋል። ሁለተኛው ደግሞ እጽዋት በሚተከሉበት ወቅት ቀደም ሲል ወደ ህዋ የሄደውን ካርበን አምቀው የሚመልሱበትን አሰራር ተግባራዊ በማድረግ እና ከልቀት የተጠበቀውን ካርበን ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እያከናወነች ባለችው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት የካርበን ሽያጭን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑንና ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር የግዢ ውል ስምምነት እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የኖርዌይ መንግስት እንደመነሻ የ75 ሚሊዮን ዶላር የካርበን ግዢ እንዲሁም የዓለም ባንክም እንዲሁ የግዢ ውል ማሰሩን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ኖርዌይ እና የዓለም ባንክ ሊገዙት ከሚፈልጉት በላይ ካርበን ማመንጨቷን ጠቁመው፤ እስከ አንድ ቢሊየን ዶላር ሊያመጣ የሚችል ካርበን ሀብት መኖሩን ገልጸዋል። በዓለም ገበያ ላይ ለካርበን ግዢ የሚመደበውን ከፍተኛ ሀብት ወደ ኢትዮጵያ የካርበን ሽያጭ ማምጣት የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። በዓለም ላይ ያለውን የካርበን ፋይናንስ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከማጠናከር ባለፈ ሰነዶች የማደራጀትና ሌሎች ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል።          
ኢትዮ ቴሌኮም ለዲጂታልና ታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ ነው
Apr 3, 2026 418
አዳማ ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎትን ከማስፋት ባሻገር ለዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ ቴሌኮም በአዳማ ከተማ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከል በመገንባት በዛሬው እለት አገልግሎት አስጀምሯል።   በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ በኢትዮጵያ የዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአዳማ ከተማ ተገንብቶ በዛሬው እለት ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከልም የዚሁ ልማት ጥረት አካል መሆኑን ጠቁመዋል። የአዳማው ማእከል በአንድ ጊዜ 12 ተሽከርካሪዎችን ቻርጅ የሚያደርግ አቅም እንዳለው ተናግረው በሌሎች አካባቢዎችም የማስፋት እቅድ መኖሩን ገልጸዋል። ኢትዮ ቴሌኮም ከፈጣንና ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎት በተጨማሪ ለዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።   በዚህም መሰረት አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ከተሞች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጀ ማድረጊያ ማዕከላትን በማስፋፋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ፤ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት ተቀርፆ አሰራርና አገልግሎቶችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ሂደት የኢትዮ ቴሌኮም አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አንስተው በከተማዋ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከል ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 332
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 262
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 563
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት።   ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።   የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው 
Mar 22, 2026 253
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
የጤና ነገር ...
Apr 3, 2026 2078
በዮሐንስ ደርበው የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። የኒውትሬሽን ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ የሰው ልጅ የሰውነት ክፍል 60 በመቶው ውኃ እንደመሆኑ ለተስተካከለ ጤና ሚዛን መጠበቅ በቂ ውኃ መጠጣት ይገባል። ውኃን በትክክለኛው መጠንና ጊዜ መውሰድ ከተቻለ የኩላሊት ህመም ተጋላጭነትን 50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ነገር ግን ሰውነት የሚፈልገውን የውኃ መጠን በአግባቡ ካላገኘ ለዕለታዊ እና በጊዜ ሂደት ሥር ለሚሰድዱ ህመሞች የመጋለጥ ዕድል እንደሚጨምርም ያነሳሉ። ለመሆኑ ሰውነት የሚፈልገውና በቂ የውኃ መጠን የሚባለው መጠኑ ስንት ነው? በቂ ውኃ አለመጠጣትስ የሚያስከትለው ችግር ምንድን ነው? በሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎች ላይ የኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ምላሽ አላቸው። አንድ ሰው የሚያስፈልገው የውኃ መጠን በዕድሜ፣ ጾታ፣ በሥራ ባሕርይ፣ በመኖርያ አካባቢ፣ እንደ ጤና ሁኔታው እና እንደ ሰውነት ክብደቱ እንደሚወሰንም በምላሻቸው አስገንዝበዋል። ለምሳሌ የስኳር ታማሚዎች፣ የምታጠባ እናት፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎች፣ ብዙ አድካሚና ላብ የሚያወጡ፣ በሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በቀን 3 ሊትር ውኃ መጠጣት አለባቸው ይላሉ። በአማካይ ግን በቀን አንድ ሰው ከ2 እስከ 3 ሊትር ውኃ መጠጣት እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። ጤናማ ሕይወት የሚመሠረተው ከውኃ ነው፤ ለምሳሌ ውኃማውን 60 በመቶ የሰውነት ክፍል ሚዛን ለማስጠበቅ የግድ አስፈላጊውን መጠን ውኃ መጠጣት እንደሚገባ ይመክራሉ። በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው ሕይወታዊ ሂደት (ባዮሎጂካል ፕሮሰስ) ውኃን መሠረት ያደረገ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ለተስተካከለ የሥርዓተ-ምግብ ሂደት፣ ቆሻሻን ከሰውነት አጣርቶ ለማስወጣት፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ሥራን ለማስተካከል እና ለሌሎችም በርካታ የሰውነት ክፍሎች የተሳለጠ ተግባር ውኃ ቁልፍ መሆኑን አንስተዋል። ይህን ተከትሎም ውኃ ካሎሪ አልባው መድኃኒት (ተፈጥሯዊው መድኃኒት) እስከመባል መድረሱን ነው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ያስረዱት። ሰውነት የሚያስፈልገውን ያህል ውኃ አለመጠጣት ግን ድካም ያስከትላል፤ ለማየት፣ ለመንቀሳቀስ፣ ለመሥራት፣ ለማሰብ፣ ለመረጋጋት . . . አያስችልምና ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንድ ሰው ውኃ የመጠማት መጠኑ ከአራት በመቶ በላይ ከሆነ ለሞት ሊጋለጥ እንደሚችልም ጠቅሰዋል። ውኃ አለመጠጣት፤ የጨጓራ ህመምን በማባባስ ማስገሳት፣ የቆዳ ድርቀትና ግርጣት፣ የኩላሊት ህመም ሌሎች የሰውነት ክፍሎችም ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ያደርጋል ነው ያሉት። ከምግብ በፊት 30 ደቂቃ ቀድሞ ውኃ መጠጣት ውፍረትን ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በቂ ውኃ ከመጠጣት በተጨማሪ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን ማዘውተር እንደሚመከርም ገልጸዋል። የፈላ ውኃ እና የዝናብ ውኃን በብዛት መጠጣት በሰውነት ውስጥ ያሉ ንጥረ ነገሮችን በማስወገድና በኩላሊት ላይም ጫና እንደሚፈጥር አመላክተዋል። ለተስተካከለ ጤናማ ሕይወት የግድ ውኃ መጠጣትን ልማድ ማድረግ እንደሚገባም ይመክራሉ። #ውኃ_መጠጣት #ጤና #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency
ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች
Apr 3, 2026 2172
በዮሐንስ ደርበው የለውጡ መንግሥት ኢትዮጵያን ማሥተዳደር ከጀመረ እነሆ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ላይ 8 ዓመት ሞላው። በእነዚህ ዓመታት በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊ ዘርፉ በዲፕሎማሲውና በሌሎችም መስኮች የተለያዩ ስኬቶች ተከናውነዋል። በእነዚህ ጥቂት ዓመታትም ለማሳካት ቀርቶ ለማሳብ የማይደፈሩ ብዙ ውጤቶችም ተመዝግበዋል። የተገኙት ስኬቶች ከጊዜያቸው የፈጠኑ ናቸው። ለዚህም ሕዝቡ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በነቂስ እየወጣ አድናቆቱን ገልጿል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰጡት የሰላ አመራርነትና ቁርጠኝነትም አክብሮቱንና ምሥጋናውን ገልጿል። የለውጡ መንግሥት አካሄድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የልማት ፕሮጀክቶችም በይበልጥ ተስፋፍተውና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መንግሥት ለሚያደርገው ጥረት ከጎኑ እንደሚቆሙም በድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተጋቧቸው መልዕክቶቻቸው አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ በለውጡ መንግሥት ለማሳካት ቀርቶ ለማሰብ የማይደፈሩ ተግባራት ተከናውነዋል። ከእነዚህ ከፍተኛ ጥቅም ከተገኘባቸው የታሪክ እጥፋትን ካሠረጹ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል ጥቂቶቹን ቀጥለን በወፍ በረር እንዳሥሣለን። ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። • የኮሪደር ልማት እንደምናውቀው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነትና ልዩ ትኩረት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከሁሉም አስቀድሞ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። አሁን ላይ ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የበርካታ ከተሞችን ገጽታ የቀየሩ አስደማሚ ሥራዎች ተከናውነውበታል። ይህም በገጠር ጭምር ተጠናክሮ የቀጠለ ጉዳይ ነው። ለዘመናት አሮጌ ገጽታዋን ይዛ ያሸለበችውን አዲስ አበባ እንደ አዲስ የፈጠራትም ይኸው ፕሮጀክት ነው። አሁን ላይ መዲናይቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን ለውጥ ዐይተው ዝም ማለት አልቻሉም። ከመደመማቸው አንጻር የዘወትር አጀንዳቸውም እያደረጓት ይገኛሉ። ይህንን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፤ ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ነው ማለታቸው ይታወሳል። ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑንንም አስረድተዋል። ከለውጡ መንግሥት ዐበይት የትኩረት መስኮች አንዱ የሆነውን የቱሪዝም ዘርፉን እንቅስቃሴ ለማሳደግም ቁልፍ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ድርብርብ ፕሮጀክት ነው የኮሪደር ልማት። • የበጋ መስኖ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የለውጡ መንግሥት ዋነኛ ትኩረቱ ነው። ለዚህም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አንዱ ማሳኪያ ሥልት አድርጎ እየተጋ ይገኛል። የበጋ መስኖ ስንዴ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ማስገባት አቁማ መላክ እንድትጀምር ያስቻለ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችና በሜካናይዜሽን ታግዞ በስፋት እየተሠራበትም ይገኛል። ከለውጡ መንግሥት ወዲህ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ምክንያት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምርታማነት ማደግና የሥራ ዕድል በመፍጠር አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብም ከፍተኛ ውጤት ተገኝቶበታል። ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ ስንዴ ላይ ባሳየችው ትጋት፤ ፍጆታዋን በራሷ ዐቅም የሸፈነችው፣ ስንዴን ከውጭ ማስገባትን ያቆመችው፤ ስንዴን ወደ ውጭ መላክ የጀመረችው በለውጡ መንግሥት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ በመሸለም ለጥረታቸው ዕውቅና መስጠቱም ይታወሳል። • መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይን ለማስፈጸም እዚያም እዚህም መንከራተት የግድ ነበር። በዚህ አያበቃምና ወረፋውም ሌላ ችግር ነው። መንግሥት በተለያዩ መድረኮች ባካሄዳቸው ሕዝባዊ ውይይቶች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉልን የሚሉ እሮሮዎች በረከቱ። መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል ሥራ ወደ ተግባር አሥገባ። በዚህም መሠረት ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ ጀመረ። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነውም አሉ። ለዚህ ቁርጠኝነታችን አንዱ ማሳያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመራቸውንም ገለጹ። እንግዲህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ ታግዘው በተሳለጠ ሂደት እንዲሰጡ በማድረግ የተገልጋይን እንግልት፣ ገንዘብ እና ጊዜ መቀነስ ያስቻለ አሠራር ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት ተደርጎም ይወሰዳል። በየከተሞቹም እየተስፋፋ ነው። • አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ አይ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ተጠቃሚ እንድትሆን ከፍተኛ ጉጉት እንዳላቸው በቁጭት በተለያዩ መድረኮች ያነሳሉ። ለዚህም መፍትሔ ዘይደው ተቋማትን ከማቋቋም ጀምሮ ለዘርፉ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ተግተዋል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂው ጋር አብሮ ለመጓዝ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን አቋቋመች። የኤ አይ ዩኒቨርሲቲ በመክፈት በግብርናው፣ በጤናው እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠርም በሂደት ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል። ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም አንስተዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ማለታቸው ይታወቃል። ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ ማስገንዘባቸውም ይታወሳል። • የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው። በዚህ ሂደት ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊታአውራሪነት ይጠቀሳል። በተደራጀና ተቋማዊ ሆኖ ባልተቆራረጠ አካሄድ እየተከናወነ ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተተከሉ ችግኞችም በየዘርፉ ተጠቃሚነት አድጓል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል። • የሌማት ትሩፋት ከመጋቢት ሥጦታዎች አንዱ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ነው። የምርት አቅርቦትን በማስፋት ለተረጋጋ ግብይት እና ለተመጣጠነ ሥርዓተ-ምግብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከት ላይም ይገኛል። ኢኒሼቲቩ ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለሀገራዊ የሥርዓተ-ምግብ መሻሻል ጉልኅ ሚና እየተጫወተ ነው። የዋጋ ንረትን በማረጋጋት፣ የምርት ስብጥርን በማሳደግና በዘላቂነት በማቅረብ ረገድም የጎላ ሚና አለው። የግድ ሰፋፊ መሬት መፈለግ ሳያሻ በትንሽ ቦታ ብዙ በማምረት ፍጆታን ከመሸፈን አልፎ ኢኮኖሚን በመደጎም እና የሥራ ዕድል በመፍጠርም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። • የቱሪስት መዳረሻ ልማት ቅርሶች እንዲጠገኑ፣ አዳዲስ ሎጂዎች እንዲገነቡ፣ በመዳረሻ ስፍራዎች መሠረተ-ልማት እንዲሟላ ያስቻሉ ተግባራት በለውጡ መንግሥት ተከናውነዋል፤ አሁንም ተጠናክሮ የቀጠለ እና ስኬታማ ኢኒሼቲቭ ነው። በዚህ ሂደት ከሐሳብ አመንጭነት ባሻገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የጻፉትን መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ ጭምር ለቅርስ ጥገናና ለቤተ-መጻሕፍት ግንባታ እንዲውል አድርገዋል። በተጨማሪም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት፤ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ ወደ ተግባር አስገብተዋል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። አማራጭ የቱሪስት መዳረሻም ሆነዋል። • የተቋማት ግንባታ ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል መሪል ሐሳብ በተካሄደው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ፤ የተቋማት ግንባታና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ብለዋል። በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ሲሉም አስገንዝበዋል በወቅቱ። ዘመን የማይለውጣቸው ዘላቂ ጠንካራ ሃገራዊ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ብዙ ርቀት መጓዝም ተችሏል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲሆኑ በማድረግ እና ሥርዓት በተለዋወጠ ቁጥር የማይፈርሱ ወይም የሚሻገሩ ተቋማት መገንባት ተችሏል። ይህ ትጋት ተጠናክሮም ቀጥሏል።
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3680
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … በኢዜአ ዐይን …! የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ 
Mar 2, 2026 437
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል።   የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 4, 2026 1108
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 20 እስከ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ስለ አዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ አዲስ አበባ ከዋና ከተማ በላይ መሆኗን ገልጸው፤ በፈጣን እንቅስቃሴ ላይ ያለች፣ ወደ ኢትዮጵያ ነገ የመግቢያ በር፣ በፍጥነት እየተለወጠች ያለች የሀገር የልብ ትርታ፣ ሁሉንም አሳታፊ እና አርቆ አሳቢ የሆነ የከተማ ልማት ትልማችን መገለጫ ናት ብለዋል። ፈጣን መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት፣ የዘመናዊ ከተማ መፍትሔዎችን በማቅረብ፣ አካታች በሆነ መልኩ መኖሪያ ቤት በመገንባት እና ዘላቂ ዕድገትን በማረጋገጥ እየሠራን ያለነው ዛሬን ብቻ ሳይሆን ለነገው ትውልድ ጭምር ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ከተሞቻችን ሰዎችን ለማብቃት፣ ዐቅምን ለመጠቀም እና ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ ቅርጽ ይዘዋልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። • አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀው ከፍተዋል። ‎በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው ብለዋል በወቅቱ። ‎የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከል ማከተቱን አብራርተዋል። ‎ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። • የአዲስ ስፖርት ፓርክ መመረቅ ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)‎ የከተማችንን እድሳት ለማፋጠን እና የዜጎቻችንን ክብር ለመመለስ የገባነውን ቃል አንዱ ማረጋገጫ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን በይፋ መርቀን ከፍተናል ብለዋል። ‎በ5 ነጥብ 7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ፕሮጀክት፤ በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ 15 አትሌቶችን የሚዘክሩ የክብር ሐውልቶችን በፓርኩ መሃል በማቆም፣ የጀግኖቻችን ታሪክ ለተተኪ ትውልድ ስፖርተኞች ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋልም ነው ያሉት። የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስና የሜዳ ቴኒስ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የ800 ሜትር የሩጫ ትራክን ጨምሮ፤ እያንዳንዱ የዚህ ማዕከል ክፍል የዓለም አቀፍ መስፈርቶችን እንዲያሟላ ተደርጎ ተገንብቷል ሲሉም ገልፀዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በአፋር ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፋር ክልል ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት በአዋሽ ወንዝ ተፋሰስ በመሥኖ እየለማ ያለው የሱፍ ምርት ለተሻገረ ግብርና እና ለተሻገረ ገጠር ራዕያችን ተደማሪ ሃብት ነው ብለዋል። በአፋር ክልል ያየነው በመሥኖ ተፋሰስ በረሃ የመሰለውን ምድር የምርት መትረፍረፊያ የማድረግ ትጋት፤ ለሌሎች በተለይም ከዓመት እስከ ዓመት ዝናብ አጠር አካባቢዎች ትልቅ የመማሪያ ሠነድ እንደሚሆን አመላክተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በተካሄደው "የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ቅንጅት ለሀገራዊ ሰላም እና ደኅንነት" በሚል መሪ ሐሳብ በተካሄደው ብሔራዊ የደኅንነት ኮንፈረንስ ላይ የተሳተፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የጸጥታና ደኅንነት ተቋሞቻችን ችግርን ወደ ዕድል እንዲቀየሩ ያስቻሉ ናቸው ብለዋል፡፡ ጉዟችን ተጀመረ እንጂ አልተቋጨምና ከትናንት ዕዳዎች ተላቀን፣ የዛሬ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን ለነገው ትውልድ የምትመጥን ሀገር ለመገንባት በዓላማ ጽናት እንቀጥላለን ሲሉም አመላክተዋል። • ስለ መጋቢት 24 መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወደ ሥልጣን የመጣውን የለውጡን መንግሥት የሚደግፉ ሕዝባዊ ሰልፎች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ሰልፎች ላይም መንግሥት ባለፉት ሥምንት ዓመታት ያመጣቸውን ለውጦች እና የተገኙ ስኬቶችን የሚያወሱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) ለሰጡት ስኬታማ አመራርነት የሚያሞግሱና የሚያመሠግኑ መልዕክቶች ተስተጋብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ቀኑን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሕዝባዊ ግፊትና ትግል ያመጣው የመጋቢት ለውጥ ኢትዮጵያን ወደ ኋላ ያስቀሩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ስብራቶችን መጠገን ያስቻሉ ሪፎርሞች የተተገበሩበት ነው ብለዋል። ለሕዝባችን የላቀ ተጠቃሚነት፣ ለሀገራችን ክብርና ብልፅግና መሳካት አበክረን እንሠራለን ሲሉም ገልጸዋል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በበኩሉ ቀኑን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በኃይልና በምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ አስደማሚ ስኬቶችን አስመዝግባለች ብሏል። የለውጡን መሠረት ከማስፋትና ከማጽናት ወደ ማላቅ የተሸጋገረችው ኢትዮጵያ፤ በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌትነቷን በተግባር ታውጃለች ሲልም ገልጿል። ይህን ለውጥ ዕውን ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ፤ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በድል እንደሚያሳርጉት ጥርጥር የለውም ነው ያለው። • የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ስምምነት የኢትዮጵያ መንግሥት በInvest in Ethiopia 2026 ፎረም፤ ከቻይና፣ ፖላንድ፣ ሕንድ፣ ሲንጋፖር እና ኬንያ ከመጡ አጋሮች ጋር የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ታሪካዊ የኢንቨስትመንት ስምምነት መፈራረሙን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት አስታውቋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማዕድንና በአረንጓዴ አሞኒያ ዘርፎች ላይ ያተኮሩት እነዚህ ስምምነቶች፤ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ጉልህ ማሳያ ናቸው ብሏል። በተመሳሳይ ጽሕፈት ቤቱ ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለውን የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ የሚተካ የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 ሆኖ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል ብሏል። የ1954 የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየ በመሆኑ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት እና ከወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዘርፉ ካሉ አዳዲስ አሠራሮችና የቴክኖሎጂ እድገቶች አኳያ ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ መልኩ መከለሱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ባለፉት ዓመታት የአዲስ ሕግ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ብዙ ምክክር ተደርጎበት የጸደቀው የሕግ መድብል አዳዲስ አሠራሮችን የሚያስተዋውቅ፤ የወንጀል ምርመራ፣ ክስና ማስረጃ ሥርዓቱን ወደአዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው ሲልም አስገንዝቧል ጽሕፈት ቤቱ።
ባሳለፍነው ሳምንት
Mar 28, 2026 505
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 13 እስከ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • ‎የ ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን እና የሰው ልጅ ታሪክ በጀመረበት ምድር የተገነባውን ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅት ሎጁ የዛሬ 50 እና 60 ዓመት መሠራት የነበረበት ቢሆንም፤ አሁን ስለዘገየን አንቆጭም ማለታቸው ይታወሳል። ይህን ስለሠራንም አንረካም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሩጫችን ገና ብዙ እንደሆነ፣ አፋር ገና እንዳልተነካ አስበን ይህን ጅማሮ ይበልጥ በማላቅ ለማስቀጠል እንተጋለን ሲሉም ተናግረዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከቃና ቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነም ገለጻ አድርገዋል። እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸውን ፋይዳም አንስተዋል። • ኢትዮጵያ በማላቦው ጉባዔ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ ወደ ማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ማላቦ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑዌል ኡሳ ኡዙዌን ጨምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጉባዔው ከመጋቢት 18 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ ሲሆን እስከ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቀጥላል። • የልማት ሥራዎች ጉብኝት በባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የባሕር ዳር ከተማን የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያጎሉና ግንባታቸው እየተፋጠኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ መሠረተ-ልማት እና የአየር መንገድ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገታችን የጎላ ፋይዳ ይኖራቸዋል ሲሉም በወቅቱ ገልጸዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጎንደርን የውኃ ጥም ይቆርጣል፤ የገበሬውን መሬት ያጠጣል፤ የአካባቢውን ምኅዳር ይለውጣል የተባለው የመገጭ የመጠጥ ውኃ ግድብ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተዋል። በዚሁ ወቅት የሀገር ሀብት ፈስሶባቸው መክነው እና ባክነው የቀሩ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ከሞት እያስነሡ ማፋጠን የዚህ መንግሥት ልዩ መለያው ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም የመገጭ ግድብ ምስክር መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ሳይና ሳቢያ የገጠር ቀበሌ የተገነቡ የገጠር ኮሪደር ሞዴል ቤቶችን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም በአንድ ወር የግንባታ ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀው ይህ ሞዴል መንደር በአካባቢው ለረጅም ዓመታት የቆየውን የጤና ጣቢያ፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎት ጥያቄ በተግባር መልሷል ብለዋል። በሀገራችን ከተማው ብቻ ሳይሆን ገጠሩም እኩል እየተዋበ፣ በልማት እየተገነባና በዕድገት ፍኖት ላይ በጽኑ መሠረት እየተራመደ ይገኛልም ነው ያሉት። ይህ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የማሸጋገር ትልቁ ማሳያችን ነው ሲሉም ገልጸዋል። • "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ በአዲስ አበባ 4ኛው "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም፤ የምንፈልገው ድጋፍን ሳይሆን አጋርነትን ነው፤ እርዳታን ሳይሆን ኢንቨስትመንትን ነው! ለባለ ሀብቶች ምቹ፣ ግልጽና ተራማጅ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ አዘጋጅተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ካፒታል፣ ለችሎታ እና ለዕድል በሯን ወለል አድርጋ መክፈቷንም አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ አሁን በፍጥነት ወደ ከፍታ እየገሠገሠች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ የዕድገት ጉዞ፤ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ባለ ሀብቶች ኢትዮጵያ ለእናንተ ዝግጁ የሆነ፣ በዕድሎችና በስኬቶች የተሞላ ታላቅ የኢንቨስትመንት መሶብ አላት፤ ኑ አብረን እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል! • የትግራይ ክልል አጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በሰጡት መግለጫም፤ ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ለመጀመርና ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል። በዚህም ከክልሉ ጊዜያዊ አሥተዳደር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀሌ እና በአዲስ አበባ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ጥረቶች ውስጥ ሂደቱን በክልሉ ለማካሄድ የሚያስችሉ አስቻይ ሁኔታዎች ባለመፈጠራቸው፤ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች ምርጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ እንዲከናወን መወሰኑንም አስረድተዋል።
ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት
Mar 26, 2026 217
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በኋላ የታዛቢነት (Observer) ደረጃን አገኝታለች። እ.ኤ.አ በ2006 የውጭ ንግድ ፖሊሲዋን የሚገልጽ ሰነድ ለድርጅቱ አቅርባለች። ሰነዱ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች፣ የወጪና ገቢ ንግድ ሕጎች፣ የቀረጥ፣ ከቀረጥ ውጭ ያሉ የንግድ ገደቦች፣ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ እና የኢንቨስትመንት ሕጎችን ያካተተ ነበር። በኢትዮጵያ እና በዓለም ንግድ ድርጅት መካከል የመጀመሪያው የድርድር ምዕራፍ የተጀመረው እ.አ.አ በ2008 ነው። ከእ.አ.አ 2008 እስከ 2012 በቆየው የቴክኒክ ድርድር ሶስት የስራ ቡድን ስብስባዎች ተካሂደዋል። በዚህ ወቅት የነበረው ድርድር በዋናነት ኢትዮጵያ ስለ ንግድ ሥርዓቷ ማብራሪያ የምትሰጥባቸው እንጂ፣ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘት አልቻሉም። ከእ.አ.አ 2012 እስከ 2019 የሁለቱ ወገኖች ድርድር ተቋርጦ ነበር፤ ለሰባት ዓመታት እንዲቋረጥ ያደረጉ የተለያዩ ምክንያቶች ይነሳሉ። በወቅቱ ስልጣን የነበረው የኢህአዴግ መንግስት "የገበያ ውድቀት" አለ ብሎ ያምን ነበር። ስለዚህም እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም እና ኢነርጂ ያሉ ስትራቴጂካዊ ዘርፎች በመንግስት እጅ መቆየት አለባቸው የሚል አቋም ነበረው። ይህ የመንግስት ጽንሰ ሀሳብ ድርጅቱ የተለያዩ ዘርፎች ለውጭ ክፍት መደረግ አለባቸው ከሚለው አቋም ጋር የሚጣጣም አልነበረም። በዓለም ንግድ ድርጅት የተጠየቁ የንግድ ስርዓትን የማዘመን ስራዎች በሚፈለገው መልኩ አለመሄዳቸውም ለድርድሩ መቆም እንደ ምክንያትነት ይነሳል። የለውጡ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ የአባልነት ድርድር በድጋሚ ነፍስ ዘርቷል። መንግስት በተለያዩ ዘርፎች የወሰዳቸው ጠንካራ የንግድ እና ኢኮኖሚ እርምጃዎች ድርድሩ በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀጥል አድርጓታል። መንግስት እንደ ቴሌኮም፣ ባንክ እና ሎጅቲክስ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉ በድርጅቱ እንደ ትልቅ ለውጥ የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያን ሕጎች ከድርጅቱ ህጎች ጋር የማጣጣም ስራም ተከናውኗል። ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለው የንግድ ሕግ ማሻሻያ ተደርጎበት ዘመናዊ የንግድ አይነቶች የተካተቱ ሲሆኑ፤ የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መቋቋም የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ላይ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል። ኢትዮጵያ የሸቀጦች ታሪፍ ቅናሽ ሰነዷን አሻሽላ አቅርባለች። ይህም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች የምትጥለው ቀረጥ በምን ያህል መጠንና በስንት ዓመት ውስጥ እንደሚቀንስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የገባችውን ቃል በተግባር ያሳየችበት ነው። በአሁኑ ሰዓት በዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ኢትዮጵያ በተናጠል እንደ ቻይና፣ ሩሲያ፣ አሜሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችና ካናዳ ካሉ ሀገራት እና ከአውሮፓ ህብረት ጋር የገበያ ተደራሽነት ድርድር እያደረገች ነው። በተደረጉት የተናጥል ድርድሮች ላይም ለኢትዮጵያ አባልነት ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። ከአዕምሯዊ ንብረት ጋር በተያያዘ የፈጠራ ውጤቶችን፣ የንግድ ምልክቶችን እና የባህል እሴቶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ ሕግና ተቋም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጓል። የጉምሩክ አሰራር የሸቀጦችን ፍሰት ለማሳለጥ የዲጂታል ጉምሩክ አሰራርን የማስፋፋት ስራ በመንግስት በኩል ተከናውኗል። 14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ስብስባ ከመጋቢት 17 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በካሜሮን ያውንዴ መካሄድ ጀምሯል። በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክም በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ያውንዴ ገብቷል። ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከስብስባው ጎን ለጎን የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን ሚኒስትሩ ከዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ (ዶ/ር) ጋር ያደረጉት ውይይትም በዋናነት የሚጠቀስ ነው። በውይይቱ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለድርጅቱ አባል አገራት ከ1200 በላይ ለሚሆኑ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠቷንና ከ419 በላይ የሕግና የፖሊሲ ይዘቶችን ማሳወቋን ጠቁመዋል። የያውንዴው ስብስባ ለኢትዮጵያ የአባልነት ጉዞ የፖለቲካ ድጋፍን ለማሰባሰብ ያስችላታል። በቅርቡ የድርጅቱ አባል ከሆኑ የአፍሪካ እና ሌሎች ሀገራት ጋር የቴክኒክ እና የተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግም ምቹ አጋጣሚ ይፈጥርላታል። የያውንዴው ውይይት ኢትዮጵያ በቴክኒክ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ ደረጃም ለድርድር ዝግጁ መሆኗን የምታሳይበት ነው። የዓለም የንግድ ድርጅት እ.አ.አ በ1995 የተቋቋመ ሲሆን ዋና መቀመጫው ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ነው።ድርጅቱ 166 አባል ሀገራት አሉት። አባል ሀገራቱ የዓለምን 98 በመቶ የንግድ ልውውጥን እንደሚሸፍኑ መረጃዎች ያመለክታሉ። የዓለም ንግድ ድርጅት በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው አቅምና ተጽዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው። ድርጅቱ ራሱ ገንዘብ የሚያበድር ባንክ ባይሆንም፣ የዓለምን የንግድ “የጨዋታ ሕግ" በመቅረጽ ረገድ ያለው ሚና ትልቅ መሆኑን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል መሆኗ የገበያ እድሏ እንዲሰፋ ያደርጋል። የኢትዮጵያ ምርቶች በ160+ አባል አገራት ገበያ ውስጥ ያለ አድሎና በዝቅተኛ ታሪፍ እንዲገቡ ዕድል ይሰጣል። ይህ በተለይም ለግብርና ውጤቶችና ለጨርቃጨርቅ ምርቶች ትልቅ በር ይከፍታል። የኢትዮጵያ አባል መሆን ሀገሪቷ ዓለም አቀፍ የንግድ ሕጎችን እንደምታከብር ማረጋገጫ ስለሚሆን፤ ትልልቅ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸው እምነት እንዲጨምር ያደርጋል። ኢትዮጵያ አባል መሆኗ ከሌሎች አገራት ጋር የንግድ አለመግባባቶች ቢገጥሟት፣ በድርጅቱ የክርክር መፍቻ መድረክ አማካኝነት መብቷን ማስከበር ትችላለች። ኢትዮጵያ የንግድ አቅሟን ለመገንባት የሚያግዙ ልዩ ልዩ ሥልጠናዎችንና የቴክኒክ ድጋፎችን ከድርጅቱ ማግኘት ትችላለች። ኢትዮጵያ በያዘችው ፍጥነት እና ቁርጠኝነት ከቀጠለች እ.አ.አ 2026 የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድሯን የማጠናቀቅ እድሏ ሰፊ ነው። የድርድሩ መጠናቀቅ ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማጽደቅ እና የአገር ውስጥ ህጎችን ከድርጅቱ ሕግ ጋር የማጣጣም ስራዎችን ጨምሮ በቀጣይ ምዕራፍ ለሚከናወኑ ስራዎች በር ይከፍታል። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን ውጥኗ ከ23 ዓመታት በኋላ እውን ሊሆን የተቃረበ ሲሆን ድርድሩም ወደ መደምደሚያው ምዕራፍ ደርሷል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 905
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል የነዳጅ ብክነትን ለመቀነስ ምን ዓይነት ብልኀት መጠቀም ይመከራል? ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3830
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2598
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8389
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6879
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60789
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54767
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35285
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32895
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27932
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27131
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26636
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26245
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60789
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54767
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35285
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32895
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች
Apr 5, 2026 4413
በዮሐንስ ደርበው ✍️ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ‘በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ’ ከሚለው ብኂል የላቁና ቁጭት የወለዳቸው ኢኒሼቲቮች - የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እንዲሁም የሥራ ዕድልን እያሳደጉ ነው። ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ እንደመሆኗ ብዙ ናት። ይህን ሁሉም ሀገራት ስለማያገኙት ዕድለኛም ናት፤ የእኛም ስለሆነች መታደል ነው። የተለያየ የኑሮ ዘይቤ፣ ባህል እንዲሁም ሁሉንም የዐየር ፀባይ ዐቅፋለች። ደግሞም ልዩ ልዩ የተፈጥሮ አቀማመጥ በልዩነት የተቸራት። አሥረጂ ማቅረብ ቢያሻ በሀገሪቱ ከፍተኛ ከሆነው ስሜን ተራራዎች እስከ ዝቅተኛው ስፍራ ዳሎል ያለውን የተፈጥሮ ፀጋ መጥቀስ ሁነኛ ምሥክር ነው። ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ✍️ የተፈጥሮ ችሮታ ለኢትዮጵያ ከብዙ ሥጦታዎቿ መካከል ብሔራዊ ፓርኮችን ብቻ ብናነሳ… የኢትዮጵያ የዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን በጀት መድቦ በቀጥታ በሥሩ 11 ብሔራዊ ፓርኮችን እና ሁለት የዱር እንስሣት መጠለያዎች ያሥተዳድራል። እነሱም፡- 📌 ስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አብያታ ሻላ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ኦሞ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አልጣሽ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ገራይሌ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ሃላይደጌ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ቃፍታ ሽራሮ ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም 👉 ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ እና 👉 ሲንቂሌ የቆርኬዎች መጠለያዎች ናቸው። ብሔራዊ ፓርኮቹና የዱር እንስሣት መጠለያዎቹ የሀገሬው ሀብት ናቸውና፤ እየተንከባከቡ መጠቀም ይገባል። ✍️ መንግሥት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ከላይ የተገለጹትን ብሔራዊ ፓርኮችና ሌሎችንም፤ ከቤት እንስሣት ንክኪ ነጻ በማድረግ፣ ከልቅ ግጦሽ እንዲሁም ከሕገ-ወጥ ዐደን ለመጠበቅ መንግሥት ብዙ ገንዘብ ያወጣል። የሰው ኃይልና የቁሳቁስ ዐቅርቦትንም ያሟላል። ይህም ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ይመሠክራል። በሌላ በኩል የላሊበላ አብያተክርስቲያናት፣ ሶፍዑመር ዋሻን እና የፋሲል አብያተ መንግሥትን ጨምሮ በየክልሎች የሚገኙ ቅርሶችን በመጠገንም እንዲሁ እየተጋ ነው። ከአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎቹ አንዱ የቱሪዝም ዘርፍ ማድረጉም ትኩረቱን ያሳያል። በዚህ ሂደት በየአካባቢው ፀጋዎችን ዕየለየ በርካታ መዳረሻዎችንና የጎብኝ ማረፊዎችን አልምቷል፤ እያለማም ነው። እነዚህም በኢኮኖሚው ብሎም በሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍ ያለ ሚና እያበረከቱ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት፤ በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ የተሠሩ መዳረሻዎችን ለአብነት ብንጠቅስ፤ ‘በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ’ ከሚለው ብኂል የላቁና ቁጭት የወለዳቸው ኢኒሼቲቮች ናቸው። የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እንዲሁም የሥራ ዕድልን እያሳደጉ ነው። ኢትዮጵያ ዛሬ ነገንም እየሠራች ነውና፤ በቱሪዝሙ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት በተለያየ የኢትዮጵያ ክፍሎች መጭውን ትውልድ ባገናዘበ ሁኔታ እየተሳለጡ ነው። በአፍሪካ መዲና በአንድነት እና የወዳጅነት ፓርኮች ጅማሮውን ያደረገው የዘርፉ ልማት፤ ወደ ወንጪ ኢኮቱሪዝም፣ ጎርጎራ፣ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት፣ የሸበሌ ሪዞርት፣ ሶፍዑመር ዋሻ፣ ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣ የዝሆኖች ዳና ሎጂ፣ የኒዒን ሌ ፓልም ሎጂ ድረስ ወዘተ… ዘልቋል። እንደቀጠለም ነው። እነዚህም ፀጋን ለይቶ ወደ ሃብት በመቀየር ሂደት በመንግሥት ብርታት የለሙ መዳረሻዎች ናቸው። መንግሥት ነባር መዳረሻዎችን በመጠገንና በማደሥ፤ አዳዲስ መዳረሻ በመገንባት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም አልሠሠተም፤ ብዙ እየሠጠ ነው። ✍️ ከቱሪዝም ዘርፍ አንጻር የሕብረተሰቡ ሚና ቱሪዝም በተፈጥሮው ከበርካታ ጉዳዮች ጋር ይተሣሠራል። በእጅጉ ሰላም ይሻል፤ የሰላም ባለቤት ደግሞ ሕዝቡ ነው። ዘርፉ የቅርሶችንና መዳረሻዎችን ልማትና እንክብካቤም ይሻል። ለዘርፉ የሚሰጥ ትኩረት ሀገርንም፤ ሕዝብንም ይጠቅማል፤ ጥቅሙ ከዕለት ጉርስ እስከ ጥሪት ይዘልቃል። በዚህ ሂደት ሕዝቡ በየአካባቢው ያሉ ብሔራዊ ፓርኮችን፣ ቅርሶችን እና የቱሪስት መዳረሻዎችን የኔ ብሎ መጠበቅ ይኖርበታል። ለምሳሌ፡- ብሔራዊ ፓርክ ወይም በመዳረሻ ላይ ጉዳት ቢደርስ በቀጥታ ተጎጂው የአካባቢው ነዋሪ ነው። ምክንያቱም ቱሪስት ካልሄደና ገቢ ካልተገኘ ገቢ ይደርቃልና።
የጀጎል አለም አቀፍ ቅርስን የታደገው ሀገራዊ ለውጥ
Apr 4, 2026 289
የስልጣኔ መነሻ የጥበብ መፍለቂያ የሆነችው የምስራቋ ፈርጥ ሀረር የንግድ፣ የፖለቲካና ማህበራዊ ትስስር ማዕከል ሆና በትውልድ ቅብብሎሽ ከአንድ ሺህ አመታት በላይ የተሻገረች እድሜ ጠገብ ከተማ ነች። በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በምስራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርትና የንግድ ማዕከል የነበረችው ከተማዋ በርካታ ቋሚና ተንቀሳቃሽ እንዲሁም የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቁሳዊና ሀይማኖታዊ ቅርሶችን የያዘች ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ ነች። ከእነዚህ ቅርሶች መካከል ጥንታዊ የስነ-ህንፃ የጥበብ፣ የከተማ ፕላን፣ ባህላዊ የመሬት አጠቃቀም፤ አካባቢያዊ መስተጋብርና የስልጠኔ መገለጫ በሚል እኤአ በ2006 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ዩኔስኮ በአለም አቀፍ ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል ቅርስ ይጠቀሳል፡፡   ቅርሱ ምንም እንኳን በኪነ ህንፃ ጥበብ በላቁ በአርቆ አሳቢ አባቶች እንዳይፈርስና ሚዛኑን ጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ በተመረጠ ድንጋይ እና አፈር በልዩ ጥበብ የተገነባ ቢሆንም በጥበቃና እንክብካቤ ጉድለት ምክንያት ከግማሽ ምዕተ አመታት በላይ እድሜን ባስቆጠረው ቅርስ ላይ አደጋ ተጋርጦበት ቆይቷል። በቅርሱ ውስጣዊ እና ውጫዊ ክፍሎች የህገ-ወጥ ግንባታዎች መበራከትና በሌሎች ምክንያቶች በደረሰበት ጉዳት የጥንት ስልጣኔ ምልክት የሆነው አለም አቀፉ የጀጎል ቅርስ ከዩኔስኮ የአለም ቅርስነት እስከመሰረዝ የደረሰ አደጋ ተደቅኖበት ነበር። ሆኖም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በአዲስ እሳቤ፤ በተደመረ አቅምና በላቀ ቁርጠኝነት፤ ህዝብን በማሳተፍ ከመንግስት ምንም አይነት በጀት ሳይመደብለት ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ማልማት ተቻለ። አሁን ላይ እነኛ በሸራና በጨርቅ በተሰሩ ህገወጥ ግንባታዎች ተወሮ የነበረው 3ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የጀጎል ግንብ ዙሪያ በአበቦችና ቅርሱን በሚያስውቡ ስራዎች ደምቀዋል።   በዚህም አባቶች ከዘመኑ ቀድመው ዛሬም ድረስ ግርምትን በሚያጭር ጥበብ አንፀው ያኖሩት ይህንን የሀገር ሀብት በመታደግ ትውልዱን ከታሪክ ተወቃሽነት ወደ ዳግም ታሪክ ሰሪነት እንዲሸጋገር ማድረግ ተችሏል። ስራውም የትላንትን መሰረት ሳያናጋ፤ የቀድሞ አባቶችን ጥበብና ስልጣኔ ሳይጋፋና ሳይዘነጋ ጥንታዊውን ከዘመናዊ ጋር አዋህዶ ቅርስ መገኛ ለሆኑ ሌሎች አካባቢዎችም ተምሳሌት በሚሆን ደረጃ አስደናቂ ስራ ተከናወነ። የአካባቢውን ሀብትና እውቀት በመጠቀም እውን የተደረገው ይህ ስራ በእያንዳንዱ የሀረሪ ጥንታዊ ቤቶች በሚገኙ የታሪክ አሻራዎችና የባህል መገለጫዎች እንዲደምቅም ሆኗል። ይህ ትውልድ ተሻጋሪ ስራ ቅርሱን ከአደጋ ከመታደግ ባለፈ ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከግለሰብ እስከ ማህበራትና የዳያስፖራ አባላት ድረስ ሁሉም በያገባኛል ስሜት አሻራውን ያኖረበት ዘመን ተሻጋሪ ፕሮጀክት ነው። ይህም በቅርሱ ላይ የእኔነት ስሜት እንዲጎለብት በማድረግ የእይታ ለውጥ እንዲመጣ ያስቻለና ቀደም ሲል የነበሩ የግለኝነት አስተሳሰቦችን በመቅረፍ የወል እሳቤ እውን የሆነበት ፕሮጀክት ሆኖ ታይቷል።   ዛሬ ላይ እነኛ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ እና በአካባቢው ለማለፍ ከባድ የነበሩ የጀጎል መንገዶች ፀድተው ውብ ሆነዋል። ይዘታቸውን ለቀው የነበሩ ቅርሶችም የአለም ቅርስነት ክብርና መስፈርትን በሚመጥን ደረጃ ታድሰዋል። ዛሬ የጀጎል ነዋሪ እንደቀድሞ አካባቢውን ለቆ ለመሄድ ሳይሆን መኖርን የሚመርጥባት የወጣውም መመለስን የሚመኝባት ምቹ አካባቢ ሆናለች። የመቻል ምልክት የትብብር ውጤትና የአብሮነት ጉልበት በተግባር የታየበት የጁገል መልሶ ልማት ጥንታውን መንደር ለነዋሪዎች ምቹ ለጎብኚዎች ተመራጭ የጉብኝት ስፍራ እንዲሆን ማድረግ ተችሏል። በለውጡ መንግስት በአዲስ መልክና ቀለም የተዋበው ጀጎል የሀረርን ቀደምት ስልጣኔ እየመሰከረ የሀገርንም ገፅታ እየገነባ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም