ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ጥናቱ በየአካባቢው ያሉ የአምራች ኢንዱስትሪ እምቅ ጸጋዎችን በማወቅና በማልማት የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር ነው
Jul 6, 2026 57
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፡- የብሔራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት በየአካባቢው ያሉ የአምራች ኢንዱስትሪ እምቅ ጸጋዎችን በማወቅና በማልማት የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ገለጹ። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የብሔራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ትግበራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሂዷል። በመድረኩ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል፤ ለሀገራት ልዕልና መለኪያው የማምረቻው ዘርፍ የደረሰበት ደረጃ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያም ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ በመሠራቱ ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረቻው ዘርፍ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን አንስተውም፤ ዘርፉ ለሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ዕድገት ያለው ድርሻ ማደጉን፣ ገቢ ምርቶችን የመተካት ሂደት መሻሻሉንና የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ማደጉን ጠቅሰዋል። የብሔራዊ አምራች ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት በሀገር አቀፍ ደረጃ በየአካባቢው የሚገኙ እምቅ ሀብቶችን፣ መሠረተ ልማቶችንና ሌሎች ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎችን የተሟላ መረጃ የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል። ይህ የተሟላ መረጃ ደግሞ በእውቀት ላይ የተመሠረተ የአምራች ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት። ጥናቱ ወደፊት ለሚከናወኑ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ትክክለኛውን አቅጣጫ የሚያመላክት ከመሆኑ በላይ፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በስፋት ለመሳብ ከፍተኛ ፋይዳ አለው ብለዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የማምረቻ ዘርፉን ለማሳደግ፣ የኑሮ ውድነት ጫናን በዘላቂነት ለመቀነስና ፈጣን የኢኮኖሚ እድገትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ የተሳተፉ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ጥናቱ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሀብቶችን ለማልማት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በጥናቱ የተመለከቱ በየአካባቢው ያሉ እድሎችን ወደ ተጨባጭ ውጤቶች መቀየር የሚያስችሉ የጋራ ሥራዎች ወሳኝ መሆናቸውን አንስተዋል። ለትግበራው ስኬታማነት ሀገር አቀፍ መረጃዎችን ከሚያሰባስቡ ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የቅንጅት ስራዎች መጠናከር እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጥናቱ ለአምራች ኢንዱስትሪው ግብዓት የሆኑትን የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች እምቅ አቅም ለመጠቀም የሀብት ልየታ መደረጉን አድንቀዋል። በአስቻይ ሁኔታም የሰው ኃይልና መሠረተ ልማትን ታሳቢ ማድረጉ ጥሩ መሆኑን አንስተው፥ ሆኖም በየጊዜው ከሚቀያየሩ ሁኔታዎች ጋር የሚጣጣም እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የማምረቻው ዘርፍ በመደመር እይታ ከፍ ያለ ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ፥ ጥናቱ የአምራች ዘርፍ ጸጋዎችን በማወቅና በመጠቀም ብልፅግናን ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል። ጥናቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉንን ሀብቶች መረጃ በአንድ ማዕከል በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ ማካተቱ ለማምረቻው ዘርፍ ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል። ጥናቱን እንደ መነሻ በመውሰድ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ መረጃዎችን በማካተት በክልሉ ለመተግበር ቁርጠኛ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በጥናቱ ሁሉን አቀፍ መረጃዎች መካተታቸው ለማምረቻው ዘርፍ ማደግ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ለባለሀብቶች በእውቀት ላይ የተመሠረተ የኢንቨስትመንት ውሳኔ ለመወሰንና ለቀጣይ የአምራች ዘርፍ ሥራዎች የተሻለ አቅም እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል። የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ፥ በሁሉም አካባቢዎች ያሉትን ሀብቶች በማካተት ተደራሽነቱን በየጊዜው እያሳደገ እንዲሄድ ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት። የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ጥናቱ በሁሉም አካባቢዎች ያለውን ተጨባጭ መረጃ ለማወቅ፣ ዘርፉ ለሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ያለውን ድርሻ ለማሳደግ፣ የምርት ግብዓትና ውጤትን ትስስር ለማጠናከር ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።
በጎንደር ከተማ ገጠር ቀበሌዎች የተጀመረው የሞዴል አርሶ አደሮች መንደር ግንባታ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jul 6, 2026 152
ጎንደር፤ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፡-በጎንደር ከተማ ገጠር ቀበሌዎች የተጀመረው ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር ግንባታ በአዲሱ በጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የከተማው አስተዳደር አስታወቀ፡፡ ከተማ አስተዳደሩ በ2019 በጀት ዓመት አሻጋሪ የእድገትና የዘላቂ የልማት እቅድ ዙሪያ ከአጋር አካላት ጋር የትውውቅ መድረክ ዛሬ አካሂዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ፕላንና ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ፋሲል አብዩ እንደተናገሩት የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ ሁለንተናዊ አገልግሎትን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት መሰረተ ልማትን በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ እና የግብርናውን ኢኮኖሚ ለማዘመንም ፋይዳው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል። በቅርቡ በጎንደር ከተማ በሳይ እና በሳቢያ የገጠር ቀበሌዎች በገጠር ኮሪደር የተገነባውን ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር በአዲሱ በጀት ዓመትም በሌሎች ቀበሌዎች ለማስፋት የቅድመ ዝግጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በአስተዳደሩ ስር በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች 20 ሞዴል የገጠር መንደሮችን ለመገንባት ዝግጅት መጀመሩንም አቶ ፋሲል ጠቅስዋል። የሚገነቡት ሞዴል መንደሮች የኤሌክትሪክ ሃይል፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ፣ መንገድና ዘመናዊ ቤቶችን የሚያካትቱ ሲሆን፣ የግንባታ ቦታ መለየትን ጨምሮ ሀብት የማፈላለግ ሥራዎችን ለማከናወን እየተሰራ ይገኛል። የሞዴል መንደሮቹ ግንባታ ለበርካታ የአካባቢው ወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸው፣ የአርሶ አደሮችንም የሥራ ባህል በመቀየር በኩል ጉልህ አስተዋጾ ያደርጋል ብለዋል። ሞዴል መንደሮቹ አርሶ አደሩ መሰረታዊ የመንግስት አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኝ ያስችሉታል ያሉት ደግሞ፣ የከተማ አስተዳደሩ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ነጻነት መንግስቴ ናቸው፡፡ መምሪያው በሞዴል መንደሮቹ ፣መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በቅርበት ለመፍታት እንደሚሰራም አመልክተዋል። በመድረኩ ላይ የጎንደር ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋ መኮንን፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ ደብሬ የኋላ እና የክፍለ ከተማ የሥራ ኃላፊዎችም ተገኝተዋል።
የአንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ
Jul 6, 2026 139
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የአንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት ተፈጽሟል። በኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ያሳረፈችው የአንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ሥርዓተ ቀብር፤ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ ወዳጅ ዘመዶቿና በርካታ የሙያ አድናቂዎቿ በተገኙበት በደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል። ከያኒዋ ካበረከተቻቸው በርካታ የሙዚቃ ሥራዎቿ መካከል "ኢትዮጵያ"፣ "አራዳ"፣ "እንደ ኢየሩሳሌም"፣ "ትዝታ"፣ "አንቺ ባለድሪ" እና "አየር ኃይላችን" የሚሉት ተጠቃሽ ሲሆኑ፤ እነዚህ ዜማዎች ዛሬም ተወዳጅነታቸው የማይደበዝዝ ድንቅ የጥበብ ሥራዎቿ ናቸው። በኪነ ጥበብ ህይወቷ በርካታ አይረሴ ድንቅ ስራዎችን ለህዝብ በማበርከት ታላቅ ባለውለታ የነበረችው አርቲስቷ፤ የሁለት ወንድና የአራት ሴት ልጆች እናት ነበረች።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ
Jul 6, 2026 202
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፡-የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከ30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ(ኮፕ 30) ፕሬዝዳንት አምባሳደር አንድሬ አራንሃ ኮሪያ ዶ ላጎ እና ከቡድናቸው ጋር ውይይት አድርገዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) አስተናጋጅ ለመሆን በምታደርገው ዝግጅት ላይ፣ ከቀደምት አዘጋጅ ሀገራት ልምድ መቅሰም ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ሆኗል። በዚህም መንፈስ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዝዳንት አምባሳደር አንድሬ አራንሃ ኮሪያ ዶ ላጎ እና ከቡድናቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የውይይቱ ዓላማ ዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ጉባኤ ከማዘጋጀት ጋር የተያያዙ ዕውቀቶችን እና የተወሰዱ ትምህርቶችን መለዋወጥ መሆኑን ተመላክቷል።
ህገወጡ የህወሓት ቡድን ሕጻናትና ሲቪሎችን በአፈሳና በግዳጅ ለጦርነት እየመለመለ ነው
Jul 6, 2026 250
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ ከህገወጥ የወርቅ ሽያጭ ሰዎችን አግቶ ወደ መሸጥ አረመኔያዊ ተግባር የገባው ህገወጡ ህወሓት በትግራይ ክልል ሲቪሎች እና ሕጻናትን እያፈሰና እያስገደደ ለጦርነት እያዘጋጀ መሆኑን ሒውማን ራይት ዋች አጋለጠ። ሒውማን ራይት ዋች ዛሬ ባወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው ሲቪሎችን ጨምሮ እድሜያቸው ገና 15 ዓመት ያልደረሱ ህጻናትን ህገወጡ የህወሃት ቡድን በግዳጅ ለውትድርና እየመለመለ ይገኛል። በመንገድ ላይ፣ በቢሮዎች ውስጥ፣ በሌሊት ከቤት ወደ ቤት በሚደረጉ ህገወጥ ፍተሻዎች እንዲሁም ለክልሉ ወጣቶች ዋነኛ የሥራ ዕድል ምንጭ ከሆኑት የወርቅ ማዕድን ማውጫ ቦታዎች ጭምር ህፃናትን እያገተ እንደሚገኝም ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ሒውማን ራይትስ ዋች ገልጿል። ቡድኑ ሲቪሎችንና ሕጻናትን በሃይል ወደ ጦርነት ለማስገባት የሚያካሂደው ዘመቻ በክልሉ የፍርሃት ድባብ እንዲፈጠር አድርጓል ብሏል ሒውማን ራይትስ ዋች በድርጅቱ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ሌቲሺያ ባደር በኩል። ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን ይህንን የግዳጅ ምልመላና በዚህ ዘመን የማይጠበቅ አረመኔያዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን የዓይን እማኞች እና የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ የቤተሰብ አባላት ያረጋገጡ ሲሆን፣ አፈናው መጠነ ሰፊና አስገዳጅ መሆኑንም መስክረዋል። የአፈናና እገታ ዘመቻው በጎዳናዎች፣ በገበያዎች እና በወርቅ ማዕድን ማውጫ ቦታዎች በተደረጉ የጅምላ አፈሳዎች ተጠናክሮ መቀጠሉም በሪፖርቱ ተገልጿል። ሒውማን ራይት ዋች ዋቢ ባደረገው መረጃ ቃለ-መጠይቅ የተደረገላቸው ሰዎች እንደተናገሩት፣ የህገወጡ ቡድን ባለሥልጣናት የቀድሞ ተዋጊዎችን ዝርዝር በመያዝ የሰፈር መረጃ አቅራቢዎችን (የሰፈር ሰላዮችን) ተጠቅመዋል ብሏል። ከዚህም አልፎ ወጣቶች ከምልመላው ለማምለጥ አካባቢያቸውን ለቀው ሲሰደዱ፣ የቡድኑ ሀላፊዎች የታዳጊዎቹን ቤተሰቦች (እናቶችን ጨምሮ) በማሰር እና በማንገላታት ቤተሰብ ላይ የጅምላ ቅጣት እየፈጸሙ መሆኑን ሪፖርቱ በስፋት አብራርቷል። ተቋሙ ባወጣው መግለጫ፤ ይህ የግዳጅ ምልመላ ድርጊት የ1949ኙን የጄኔቫ ስምምነት የሚጥስ እና በተለይም ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎችን በጦርነት ውስጥ ማሳተፍ የጦር ወንጀል መሆኑን አሳስቧል። የአፍሪካ ኅብረትን ጨምሮ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የሚደግፉ እንደ አሜሪካ፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ ኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ ያሉ ሀገራት፤ የቡድኑን የግዳጅ ምልመላ በአስቸኳይ እንዲያቆሙ እና የታፈኑ ሕጻናትንም እንዲለቁ ጠንካራ ጫና ሊያደርጉ እንደሚገባ ሂውማን ራይትስ ዎች አሳስቧል።
ፖለቲካ
ህገወጡ የህወሓት ቡድን ሕጻናትና ሲቪሎችን በአፈሳና በግዳጅ ለጦርነት እየመለመለ ነው
Jul 6, 2026 250
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ ከህገወጥ የወርቅ ሽያጭ ሰዎችን አግቶ ወደ መሸጥ አረመኔያዊ ተግባር የገባው ህገወጡ ህወሓት በትግራይ ክልል ሲቪሎች እና ሕጻናትን እያፈሰና እያስገደደ ለጦርነት እያዘጋጀ መሆኑን ሒውማን ራይት ዋች አጋለጠ። ሒውማን ራይት ዋች ዛሬ ባወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው ሲቪሎችን ጨምሮ እድሜያቸው ገና 15 ዓመት ያልደረሱ ህጻናትን ህገወጡ የህወሃት ቡድን በግዳጅ ለውትድርና እየመለመለ ይገኛል። በመንገድ ላይ፣ በቢሮዎች ውስጥ፣ በሌሊት ከቤት ወደ ቤት በሚደረጉ ህገወጥ ፍተሻዎች እንዲሁም ለክልሉ ወጣቶች ዋነኛ የሥራ ዕድል ምንጭ ከሆኑት የወርቅ ማዕድን ማውጫ ቦታዎች ጭምር ህፃናትን እያገተ እንደሚገኝም ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ሒውማን ራይትስ ዋች ገልጿል። ቡድኑ ሲቪሎችንና ሕጻናትን በሃይል ወደ ጦርነት ለማስገባት የሚያካሂደው ዘመቻ በክልሉ የፍርሃት ድባብ እንዲፈጠር አድርጓል ብሏል ሒውማን ራይትስ ዋች በድርጅቱ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ሌቲሺያ ባደር በኩል። ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን ይህንን የግዳጅ ምልመላና በዚህ ዘመን የማይጠበቅ አረመኔያዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን የዓይን እማኞች እና የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ የቤተሰብ አባላት ያረጋገጡ ሲሆን፣ አፈናው መጠነ ሰፊና አስገዳጅ መሆኑንም መስክረዋል። የአፈናና እገታ ዘመቻው በጎዳናዎች፣ በገበያዎች እና በወርቅ ማዕድን ማውጫ ቦታዎች በተደረጉ የጅምላ አፈሳዎች ተጠናክሮ መቀጠሉም በሪፖርቱ ተገልጿል። ሒውማን ራይት ዋች ዋቢ ባደረገው መረጃ ቃለ-መጠይቅ የተደረገላቸው ሰዎች እንደተናገሩት፣ የህገወጡ ቡድን ባለሥልጣናት የቀድሞ ተዋጊዎችን ዝርዝር በመያዝ የሰፈር መረጃ አቅራቢዎችን (የሰፈር ሰላዮችን) ተጠቅመዋል ብሏል። ከዚህም አልፎ ወጣቶች ከምልመላው ለማምለጥ አካባቢያቸውን ለቀው ሲሰደዱ፣ የቡድኑ ሀላፊዎች የታዳጊዎቹን ቤተሰቦች (እናቶችን ጨምሮ) በማሰር እና በማንገላታት ቤተሰብ ላይ የጅምላ ቅጣት እየፈጸሙ መሆኑን ሪፖርቱ በስፋት አብራርቷል። ተቋሙ ባወጣው መግለጫ፤ ይህ የግዳጅ ምልመላ ድርጊት የ1949ኙን የጄኔቫ ስምምነት የሚጥስ እና በተለይም ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎችን በጦርነት ውስጥ ማሳተፍ የጦር ወንጀል መሆኑን አሳስቧል። የአፍሪካ ኅብረትን ጨምሮ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የሚደግፉ እንደ አሜሪካ፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ ኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ ያሉ ሀገራት፤ የቡድኑን የግዳጅ ምልመላ በአስቸኳይ እንዲያቆሙ እና የታፈኑ ሕጻናትንም እንዲለቁ ጠንካራ ጫና ሊያደርጉ እንደሚገባ ሂውማን ራይትስ ዎች አሳስቧል።
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎች የወጣቶችን የተሻለች ሀገር ግንባታ መሻት ታሳቢ ያደረጉ ናቸው
Jul 6, 2026 251
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎች የወጣቶችን የተሻለች ሀገር ግንባታ መሻት ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን የወጣት አደረጃጀት ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን በስልጡን የምክክር መፍትሔ ለመስጠት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሰናድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ከሚቀጥለው ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሂደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤም ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደርና ሰላም ግንባታም የምክክር ሂደቱ ዐበይት አጀንዳዎች ናቸው። የዮቡንቱ ወጣቶች ለሰላም ጥምረት ሰብሳቢና የጣምራ ማህበራዊ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ይርጋለም ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር ቁልፍ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በተጀመረ ማግስትም የወጣቶችን ተሳትፎና ግንዛቤ በማሳደግ በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ምዕራፍ ገንቢ ሚና መወጣታቸውን ገልጿል። የምክክር ሂደቱ አሳታፊና አካታችነትም ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ዘላቂ ሀገራዊ መግባባትና ዕድገትን ለማሳለጥ የሚያስችል የታሪክ አጋጣሚ መሆኑን ተናግሯል። ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ ወጣቶች ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያስረከቧቸው አጀንዳዎችም በዋናው ጉባኤ በሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ሥር በንዑስ አጀንዳነት መካተታቸውን አንስቷል። ይህም ሀገራዊ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን በመገንባት ወጣቶች በሀገራቸው የዘላቂ ሰላም ግንባታና ልማት የሚኖራቸውን ገንቢ ሚና የሚያሳይ መሆኑን አስረድቷል። በዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎችም ዘላቂ ሰላምና መግባባትን ለመፍጠር እንደሚረዱ በመጥቀስ፤ የዋናው ጉባኤ የህዝብ ተወካዮችም በኃላፊነት መንፈስ መመካከር እንዳለባቸው አስገንዝቧል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት በረከት ብርቢርሳ በበኩላቸው፤ በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ምዕራፍ የወጣቶች ተሳትፎ የተረጋገጠበት ነው ብሏል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርም የዘመናት የተዛቡ ትርክቶችንና የሀገራዊ መግባባት መዛነፎችን በማረቅ የወጣቶችን ዘላቂ ሰላምና ዕድገትን የሚያሳልጥ መግባባት ለመገንባት ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጿል። የእስካሁኑ የሀገራዊ ምክክር ሂደት አካታችና አሳታፊነትም ወጣቶች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ የመፍትሔ አካል መሆናቸውን በተግባር እንዳስመሰከረ ተናግሯል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ጉባኤ ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችም የተናጠል ፍላጎት ማስፈጸሚያ ሳይሆኑ በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚያስችሉ መሆናቸውን አንስቷል። በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተለዩ ዐበይት አጀንዳዎችም የሀገርን ችግር ክብደትና ቅለት ታሳቢ በማድረግ የተቀረጹና የወጣቶች የተሻለ ሀገር ግንባታ መሻት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አስገንዝቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ
Jul 6, 2026 352
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርቡ ተገለጸ፡፡ በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 55 ንዑስ አንቀፅ 17 እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 81 ንዑስ አንቀፅ 1 እና 3 መሠረት የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና ሌሎች የፌዴራሉ መንግሥት ባለስልጣናትን ለጥያቄ የመጥራትና የሕግ አስፈፃሚውን አካል አሠራር የመመርመር፣ የመከታተልና የመቆጣጠር ሥልጣን አለው፡፡ በዚሁ ሕገ መንግሥትና የምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ መሠረት 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው 30ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምክር ቤቱ ተገኝተው የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት ዓመታዊ በጀት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ በተያያዘም ምክር ቤቱ ፣ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን እንደሚያፀደቅ ይጠበቃል፡፡
በኢትዮጵያ እያደገ የመጣው የፖለቲካ ተሳትፎና የምርጫ ሂደት ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት የሚያስችል ጥሩ መሰረት እያኖረ ነው
Jul 6, 2026 343
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየጎለበተ የመጣው የፖለቲካ ተሳትፎና የምርጫ ሂደት ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት የሚያስችል ጥሩ መሰረት እያኖረ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በምርጫው የተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አብላጫ የምክር ቤት ድምፅ ላገኘው ብልጽግና ፓርቲ የመልካም ምኞት መልዕክቶች ማስተላለፋቸው ይታወሳል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቶች ባስተላለፉት መልዕክት ምርጫው ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ አሳታፊ እና አካታች በሆነ መልኩ ጠንካራ ፉክክርና የላቀ የህዝብ ተሳትፎ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲዎች በሃሳብ የበላይነት የተፎካከሩበትና በሰለጠነ አግባብ ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ጥሩ መሰረት እያስቀመጠ መሆኑን አመራሮቹ ይናገራሉ። ከምርጫ ፉክክሩ ማግስት ጀምሮ የህዝብን ውሳኔ የመቀበል ዝግጁነትን ከማሳየት ባለፈ በትብብር ሀገረ መንግስት የመገንባትና ለሀገር ብሄራዊ ጥቅም መከበር ጠንካራ አቋም ይዞ የመስራት ልምድ እየዳበረ መምጣቱን ገልጸዋል። ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች መካከል የኦሮሚያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ተወካይ ታሪኩ ድንበሩ፤ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ተሳትፎና የምርጫ ሂደት መሰረታዊ ለውጥ የመጣበት መሆኑን ተናግረዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የነበረው አጠቃላይ የምርጫ ሂደትም ይህንኑ በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸው ፉክክሩ ከተጠናቀቀ በኋላ የምርጫ ቦርድን ውጤት በመቀበል በቀጣይ በትብብር ሀገር ለመገንባት በጋራ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሰው ሀብት አስተዳደር ኃላፊ ኤርሚያስ ተገኔ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የተሟላ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ከምርጫ በኋላም ሀገር የምትቀጥል በመሆኑ ሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል ማራመድ እንዳለባቸው አንስተው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቀጣይነት እንዲኖረው ፓርቲያችን የበኩሉን ኃላፊነት መወጣቱን ይቀጥላል ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሞገስ ኢደኤ፤ በኢትዮጵያ የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰለጠነ አግባብ መሰረታዊ የፖለቲካ ባህል ለውጥ ያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በሕዝብ ድምፅና በሀሳብ ልዕልና ብቻ ሥልጣን መያዝ እንደሚቻል በማመን ከፉክክር ማግስት ውጤቱን በመቀበል በትብብር ሀገር ግንባታ ላይ ጠንካራ ተሳትፎ እያሳዩ መሆኑን ተናግረዋል።
ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ማካሄድ የሚያስችል በቂ ዝግጅት ተደርጓል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jul 6, 2026 383
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ ዋናውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ማካሄድ የሚያስችል በቂ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ ከሐምሌ ስምንት ጀምሮ የሚካሄደውን ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ በአዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በሚካሄደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤ ከወረዳ፣ ክልል፣ ፌዴራልና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በድምሩ 4 ሺህ ተወካዮች እንደሚታደሙ አስታውቀዋል። ለዋናው ጉባኤ ተሳታፊዎችም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ምቹና አስተማማኝ የሕፃናት ማቆያ፣ ትራንስፖርት፣ ጤና፣ ምግብ፣ የማረፊያና ልዩ ልዩ የአገልግሎት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። የመሰብሰቢያና የመመካከሪያ ስፍራዎች ለአካል ጉዳተኞች፣ ለአቅመ ደካሞችና ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ተሳታፊዎች ምቹ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ልዩ ዝግጅት መደረጉንም አስረድተዋል። የዋናው ጉባኤ ተሳታፊዎችም በምክክር ጊዜ ቆይታቸው ምንም ዓይነት የመስተንግዶ ክፍተት እንደማይኖር አረጋግጠዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓትም በልዩ መርሃ ግብርና ሀገራዊ አንደምታውን በሚመጥን መልኩ ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል። የምክክር ሂደቱ ሥነ-ዘዴ መሠረትም ተሳታፊዎች በተለያዩ የምክክር ቡድኖች ሆነው በአጀንዳዎች ላይ ጥልቀት ያለው ምክክር በማድረግ መግባባት ላይ ለመድረስ የሚረዱ የመመካከሪያ ሥፍራ ዝግጅቶች ተጠናቅቀዋል ብለዋል። በአጠቃላይም ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከ ዳር በተወካዮቻቸው አማካኝነት እጅግ መሠረታዊና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚመክሩበት ታላቅ መድረክን ስኬታማ የሚያደርጉ ተግባራት መሠራታቸውን አረጋግጠዋል። በመሆኑም የጉባኤው ተሳታፊዎች እየተላለፈ ባለው ጥሪ መሠረት እስከ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ አዲስ አበባ ከተማ በመግባት ለኮሚሽኑ ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴዎችን የእቅድ አፈጻጸም መርምሮ አጸደቀ
Jul 6, 2026 351
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፦የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴዎችን የእቅድ አፈጻጸም መርምሮ አጽድቋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል። ምክር ቤቱ በጠዋት ውሎው፤ የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ እንዲሁም የሕገ-መንግሥት ትርጉምና ውሳኔ አፈጻጸም ክትትል ቋሚ ኮሚቴዎችን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት መርምሮና ተወያይቶ አጽድቋል። የምክር ቤቱ አባላት ቋሚ ኮሚቴዎቹ ባቀረቡት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቶች ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን ያቀረቡ ሲሆን፣ የኮሚቴዎቹ አመራሮችም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር የቀረቡት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቶች እንዲጸድቁ ለድምፅ ያቀረቡ ሲሆን፣ ምክር ቤቱም በሙሉ ድምፅ አጽድቋቸዋል።
በአስተዳደሩ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተቀናጀ መንገድ በመፍታት በኩል ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል
Jul 6, 2026 397
ድሬዳዋ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ አስተዳደር የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በተቀናጀ አሰራር በመመለስ በኩል ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር አስታወቁ። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ ዓመት 12ኛ መደበኛ ጉባዔውን እያካሄደ ነው። ከንቲባ ከድር ጁሃር የአስተዳደሩን የአስፈፃሚና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የ2018 በጀት አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለምክር ቤቱ እያቀረቡ ይገኛሉ። በሪፖርታቸው እንደገለፁትም፤ የአስተዳደሩን ነዋሪዎች መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተቀናጀ መንገድ ለመፍታት በትኩረት ተሰርቷል። ዘንድሮን ጨምሮ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራት እነዚህን ጥያቄዎች ከመመለስ አኳያ ተጨባጭ ውጤቶች የተገኙባቸው መሆናቸውን አንስተዋል። በተለይ ህብረተሰቡን ወደ አምራችነት ለማሸጋገር የተከናወኑ የመሠረተ ልማት አውታሮች፣ የአነስተኛ መስኖና የውሃ ፕሮጀክቶች የገጠሩን ህብረተሰብ ጥያቄዎች በተጨባጭ የመለሱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል እየተሰጡ የሚገኙ ፈጣን አገልግሎቶች የዘመናት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መፍታት ማስቻላቸውንም ነው የተናገሩት። በኮሪደር ልማት የተከናወኑት የተቀናጁ ልማቶችም ከተማዋን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል ነው ያሉት። ባለፉት ዓመታት በኢንቨስትመት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የከተማዋን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከልነት እያረጋገጡ መሆናቸውንም አንስተው እነዚህን ውጤታማና ተጨባጭ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማድረሱ ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ ዓመት 12ኛ መደበኛ ጉባዔው ከንቲባው ባቀረቡት የዕቅድ አፈፃፀም ላይ ተወያይቶ ሪፖርቱን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል። ለሁለት ቀናት የሚካሄደው ጉባዔው ከሪፖርቱ በተጨማሪ ለምክር ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማትን የዕቅድ አፈፃፃምና የድሬዳዋ አስተዳደር የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።
ባገኘነው ዕውቀት ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በመጠቀም ሀገራችንን ለማገልገል ተዘጋጅተናል
Jul 5, 2026 1102
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 28 /2018(ኢዜአ) ፦ያገኘነው ዕውቀት ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በተሻለ መንገድ እንድንረዳው አድርጎናል፤ ይህን ተጠቅመን ሀገራችንን ለማገልገል ተዘጋጅተናል ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ተመራቂዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተመራቂዎች አስመርቋል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመራቂዎች እንደገለጹት፤ በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ የተሰጣቸው ሥልጠና ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል የኢፌዴሪ አየር ኃይል የ3ኛ አየር ምደብ ምክትል አዛዥ እና የተዋጊ ሄሊኮፕተር አብራሪና አስተማሪ ኮሎኔል ደረስ እንዳለ እንደገለጹት፤ በኮሌጁ ያካበቱት እውቀት ሀገሪቱ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን በግልጽ ለመረዳትና ለመተንተን የሚያስችል ከፍተኛ አቅም ፈጥሮላቸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ የምትገኝበት የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን ተለዋዋጭ ሁኔታ በውል ለመረዳት ማስቻሉን ገልጸው፤ ይህንን ስትራቴጂካዊ ዕይታ መሠረት በማድረግ ሀገራቸው የምትሰንቀውን ታላቅ ህልምና ግብ ለማሳካት በቁርጠኝነት ለመስራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል። ሌላው አስተያየታቸውን የሰጡት ከመከላከያ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ሌተናል ኮሎኔል ዶክተር ቴዎድሮስ ገብረ ሩፋኤል በበኩላቸው፤ በስትራቴጂክና ደኅንነት ጉዳዮች ላይ የተከታተሉት ትምህርት ዘርፈ-ብዙ ሁኔታዎችን በጥልቀት ለመተንተን ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የበዙበት መሆኑን አመልክተው፤ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በትብብር መንፈስ የሚንቀሳቀሱ ከሆነ የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ በጎ ውጤት እንደሚያስገኙ አመልክተዋል። ሌላው ሰልጣኝ ከአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የመጡት አቶ ጌታሰው ደሴ እንዳሉት፤ ሥልጠናው ለሀገር አንድነት፣ ለሀገር ፋይዳ እና ለተቋማት ግንባታ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አስተዋጽኦ ለማበርከት ትልቅ አቅምና ወደፊት ለሚሰማሩበት የሥራ መስክም ስንቅ እንደሆናቸው ገልጸዋል። በተመሳሳይ ከልዩ ዘመቻዎች እዝ የመጡት ሌተናል ኮሎኔል ደረጀ ዳባሳ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ያገኙት ዕውቀት የእለት ተእለት ተግባራቸውና ከሙያቸው ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ስትራቴጂካዊ አካባቢውን፣ ጂኦፖለቲካውን እና አጠቃላይ ሁኔታውን በተገቢው መንገድ ለመረዳት አስችሏቸዋል። ትምህርቱ ለተግባራዊ ስራቸው ጠንካራ መነሻ ከመሆኑም በላይ፣ ባላቸው የረጅም ጊዜ ልምድ ላይ ትልቅ አቅም የገነባ መሆኑንም አክለዋል። የኮሌጁ ሰልጣኝ የሆኑት ኮሎኔል እማምር አያሌው በበኩላቸው፤ ቀጣናዊና የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ በደንብ በመረዳት መተንተን የሚችል ጠንካራ ሰራዊት እየተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም በአስተሳሰብ የበሰለ፣ በስትራቴጂካዊ እውቀት የዳበረና ለማንኛውም ሀገራዊ ግዳጅ ዝግጁ የሆነ ሠራዊት መገንባቱን ጠቁመዋል፡፡
ፖለቲካ
ህገወጡ የህወሓት ቡድን ሕጻናትና ሲቪሎችን በአፈሳና በግዳጅ ለጦርነት እየመለመለ ነው
Jul 6, 2026 250
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ ከህገወጥ የወርቅ ሽያጭ ሰዎችን አግቶ ወደ መሸጥ አረመኔያዊ ተግባር የገባው ህገወጡ ህወሓት በትግራይ ክልል ሲቪሎች እና ሕጻናትን እያፈሰና እያስገደደ ለጦርነት እያዘጋጀ መሆኑን ሒውማን ራይት ዋች አጋለጠ። ሒውማን ራይት ዋች ዛሬ ባወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው ሲቪሎችን ጨምሮ እድሜያቸው ገና 15 ዓመት ያልደረሱ ህጻናትን ህገወጡ የህወሃት ቡድን በግዳጅ ለውትድርና እየመለመለ ይገኛል። በመንገድ ላይ፣ በቢሮዎች ውስጥ፣ በሌሊት ከቤት ወደ ቤት በሚደረጉ ህገወጥ ፍተሻዎች እንዲሁም ለክልሉ ወጣቶች ዋነኛ የሥራ ዕድል ምንጭ ከሆኑት የወርቅ ማዕድን ማውጫ ቦታዎች ጭምር ህፃናትን እያገተ እንደሚገኝም ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ሒውማን ራይትስ ዋች ገልጿል። ቡድኑ ሲቪሎችንና ሕጻናትን በሃይል ወደ ጦርነት ለማስገባት የሚያካሂደው ዘመቻ በክልሉ የፍርሃት ድባብ እንዲፈጠር አድርጓል ብሏል ሒውማን ራይትስ ዋች በድርጅቱ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ሌቲሺያ ባደር በኩል። ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን ይህንን የግዳጅ ምልመላና በዚህ ዘመን የማይጠበቅ አረመኔያዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን የዓይን እማኞች እና የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ የቤተሰብ አባላት ያረጋገጡ ሲሆን፣ አፈናው መጠነ ሰፊና አስገዳጅ መሆኑንም መስክረዋል። የአፈናና እገታ ዘመቻው በጎዳናዎች፣ በገበያዎች እና በወርቅ ማዕድን ማውጫ ቦታዎች በተደረጉ የጅምላ አፈሳዎች ተጠናክሮ መቀጠሉም በሪፖርቱ ተገልጿል። ሒውማን ራይት ዋች ዋቢ ባደረገው መረጃ ቃለ-መጠይቅ የተደረገላቸው ሰዎች እንደተናገሩት፣ የህገወጡ ቡድን ባለሥልጣናት የቀድሞ ተዋጊዎችን ዝርዝር በመያዝ የሰፈር መረጃ አቅራቢዎችን (የሰፈር ሰላዮችን) ተጠቅመዋል ብሏል። ከዚህም አልፎ ወጣቶች ከምልመላው ለማምለጥ አካባቢያቸውን ለቀው ሲሰደዱ፣ የቡድኑ ሀላፊዎች የታዳጊዎቹን ቤተሰቦች (እናቶችን ጨምሮ) በማሰር እና በማንገላታት ቤተሰብ ላይ የጅምላ ቅጣት እየፈጸሙ መሆኑን ሪፖርቱ በስፋት አብራርቷል። ተቋሙ ባወጣው መግለጫ፤ ይህ የግዳጅ ምልመላ ድርጊት የ1949ኙን የጄኔቫ ስምምነት የሚጥስ እና በተለይም ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎችን በጦርነት ውስጥ ማሳተፍ የጦር ወንጀል መሆኑን አሳስቧል። የአፍሪካ ኅብረትን ጨምሮ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የሚደግፉ እንደ አሜሪካ፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ ኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ ያሉ ሀገራት፤ የቡድኑን የግዳጅ ምልመላ በአስቸኳይ እንዲያቆሙ እና የታፈኑ ሕጻናትንም እንዲለቁ ጠንካራ ጫና ሊያደርጉ እንደሚገባ ሂውማን ራይትስ ዎች አሳስቧል።
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎች የወጣቶችን የተሻለች ሀገር ግንባታ መሻት ታሳቢ ያደረጉ ናቸው
Jul 6, 2026 251
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎች የወጣቶችን የተሻለች ሀገር ግንባታ መሻት ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን የወጣት አደረጃጀት ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን በስልጡን የምክክር መፍትሔ ለመስጠት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሰናድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ከሚቀጥለው ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሂደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤም ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደርና ሰላም ግንባታም የምክክር ሂደቱ ዐበይት አጀንዳዎች ናቸው። የዮቡንቱ ወጣቶች ለሰላም ጥምረት ሰብሳቢና የጣምራ ማህበራዊ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ይርጋለም ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር ቁልፍ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በተጀመረ ማግስትም የወጣቶችን ተሳትፎና ግንዛቤ በማሳደግ በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ምዕራፍ ገንቢ ሚና መወጣታቸውን ገልጿል። የምክክር ሂደቱ አሳታፊና አካታችነትም ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ዘላቂ ሀገራዊ መግባባትና ዕድገትን ለማሳለጥ የሚያስችል የታሪክ አጋጣሚ መሆኑን ተናግሯል። ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ ወጣቶች ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያስረከቧቸው አጀንዳዎችም በዋናው ጉባኤ በሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ሥር በንዑስ አጀንዳነት መካተታቸውን አንስቷል። ይህም ሀገራዊ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን በመገንባት ወጣቶች በሀገራቸው የዘላቂ ሰላም ግንባታና ልማት የሚኖራቸውን ገንቢ ሚና የሚያሳይ መሆኑን አስረድቷል። በዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎችም ዘላቂ ሰላምና መግባባትን ለመፍጠር እንደሚረዱ በመጥቀስ፤ የዋናው ጉባኤ የህዝብ ተወካዮችም በኃላፊነት መንፈስ መመካከር እንዳለባቸው አስገንዝቧል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት በረከት ብርቢርሳ በበኩላቸው፤ በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ምዕራፍ የወጣቶች ተሳትፎ የተረጋገጠበት ነው ብሏል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርም የዘመናት የተዛቡ ትርክቶችንና የሀገራዊ መግባባት መዛነፎችን በማረቅ የወጣቶችን ዘላቂ ሰላምና ዕድገትን የሚያሳልጥ መግባባት ለመገንባት ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጿል። የእስካሁኑ የሀገራዊ ምክክር ሂደት አካታችና አሳታፊነትም ወጣቶች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ የመፍትሔ አካል መሆናቸውን በተግባር እንዳስመሰከረ ተናግሯል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ጉባኤ ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችም የተናጠል ፍላጎት ማስፈጸሚያ ሳይሆኑ በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚያስችሉ መሆናቸውን አንስቷል። በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተለዩ ዐበይት አጀንዳዎችም የሀገርን ችግር ክብደትና ቅለት ታሳቢ በማድረግ የተቀረጹና የወጣቶች የተሻለ ሀገር ግንባታ መሻት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አስገንዝቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ
Jul 6, 2026 352
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርቡ ተገለጸ፡፡ በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 55 ንዑስ አንቀፅ 17 እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 81 ንዑስ አንቀፅ 1 እና 3 መሠረት የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና ሌሎች የፌዴራሉ መንግሥት ባለስልጣናትን ለጥያቄ የመጥራትና የሕግ አስፈፃሚውን አካል አሠራር የመመርመር፣ የመከታተልና የመቆጣጠር ሥልጣን አለው፡፡ በዚሁ ሕገ መንግሥትና የምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ መሠረት 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው 30ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምክር ቤቱ ተገኝተው የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት ዓመታዊ በጀት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ በተያያዘም ምክር ቤቱ ፣ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን እንደሚያፀደቅ ይጠበቃል፡፡
በኢትዮጵያ እያደገ የመጣው የፖለቲካ ተሳትፎና የምርጫ ሂደት ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት የሚያስችል ጥሩ መሰረት እያኖረ ነው
Jul 6, 2026 343
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየጎለበተ የመጣው የፖለቲካ ተሳትፎና የምርጫ ሂደት ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት የሚያስችል ጥሩ መሰረት እያኖረ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በምርጫው የተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አብላጫ የምክር ቤት ድምፅ ላገኘው ብልጽግና ፓርቲ የመልካም ምኞት መልዕክቶች ማስተላለፋቸው ይታወሳል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቶች ባስተላለፉት መልዕክት ምርጫው ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ አሳታፊ እና አካታች በሆነ መልኩ ጠንካራ ፉክክርና የላቀ የህዝብ ተሳትፎ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲዎች በሃሳብ የበላይነት የተፎካከሩበትና በሰለጠነ አግባብ ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ጥሩ መሰረት እያስቀመጠ መሆኑን አመራሮቹ ይናገራሉ። ከምርጫ ፉክክሩ ማግስት ጀምሮ የህዝብን ውሳኔ የመቀበል ዝግጁነትን ከማሳየት ባለፈ በትብብር ሀገረ መንግስት የመገንባትና ለሀገር ብሄራዊ ጥቅም መከበር ጠንካራ አቋም ይዞ የመስራት ልምድ እየዳበረ መምጣቱን ገልጸዋል። ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች መካከል የኦሮሚያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ተወካይ ታሪኩ ድንበሩ፤ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ተሳትፎና የምርጫ ሂደት መሰረታዊ ለውጥ የመጣበት መሆኑን ተናግረዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የነበረው አጠቃላይ የምርጫ ሂደትም ይህንኑ በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸው ፉክክሩ ከተጠናቀቀ በኋላ የምርጫ ቦርድን ውጤት በመቀበል በቀጣይ በትብብር ሀገር ለመገንባት በጋራ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሰው ሀብት አስተዳደር ኃላፊ ኤርሚያስ ተገኔ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የተሟላ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ከምርጫ በኋላም ሀገር የምትቀጥል በመሆኑ ሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል ማራመድ እንዳለባቸው አንስተው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቀጣይነት እንዲኖረው ፓርቲያችን የበኩሉን ኃላፊነት መወጣቱን ይቀጥላል ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሞገስ ኢደኤ፤ በኢትዮጵያ የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰለጠነ አግባብ መሰረታዊ የፖለቲካ ባህል ለውጥ ያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በሕዝብ ድምፅና በሀሳብ ልዕልና ብቻ ሥልጣን መያዝ እንደሚቻል በማመን ከፉክክር ማግስት ውጤቱን በመቀበል በትብብር ሀገር ግንባታ ላይ ጠንካራ ተሳትፎ እያሳዩ መሆኑን ተናግረዋል።
ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ማካሄድ የሚያስችል በቂ ዝግጅት ተደርጓል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jul 6, 2026 383
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ ዋናውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ማካሄድ የሚያስችል በቂ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ ከሐምሌ ስምንት ጀምሮ የሚካሄደውን ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ በአዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በሚካሄደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤ ከወረዳ፣ ክልል፣ ፌዴራልና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በድምሩ 4 ሺህ ተወካዮች እንደሚታደሙ አስታውቀዋል። ለዋናው ጉባኤ ተሳታፊዎችም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ምቹና አስተማማኝ የሕፃናት ማቆያ፣ ትራንስፖርት፣ ጤና፣ ምግብ፣ የማረፊያና ልዩ ልዩ የአገልግሎት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። የመሰብሰቢያና የመመካከሪያ ስፍራዎች ለአካል ጉዳተኞች፣ ለአቅመ ደካሞችና ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ተሳታፊዎች ምቹ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ልዩ ዝግጅት መደረጉንም አስረድተዋል። የዋናው ጉባኤ ተሳታፊዎችም በምክክር ጊዜ ቆይታቸው ምንም ዓይነት የመስተንግዶ ክፍተት እንደማይኖር አረጋግጠዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓትም በልዩ መርሃ ግብርና ሀገራዊ አንደምታውን በሚመጥን መልኩ ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል። የምክክር ሂደቱ ሥነ-ዘዴ መሠረትም ተሳታፊዎች በተለያዩ የምክክር ቡድኖች ሆነው በአጀንዳዎች ላይ ጥልቀት ያለው ምክክር በማድረግ መግባባት ላይ ለመድረስ የሚረዱ የመመካከሪያ ሥፍራ ዝግጅቶች ተጠናቅቀዋል ብለዋል። በአጠቃላይም ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከ ዳር በተወካዮቻቸው አማካኝነት እጅግ መሠረታዊና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚመክሩበት ታላቅ መድረክን ስኬታማ የሚያደርጉ ተግባራት መሠራታቸውን አረጋግጠዋል። በመሆኑም የጉባኤው ተሳታፊዎች እየተላለፈ ባለው ጥሪ መሠረት እስከ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ አዲስ አበባ ከተማ በመግባት ለኮሚሽኑ ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴዎችን የእቅድ አፈጻጸም መርምሮ አጸደቀ
Jul 6, 2026 351
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፦የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴዎችን የእቅድ አፈጻጸም መርምሮ አጽድቋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል። ምክር ቤቱ በጠዋት ውሎው፤ የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ እንዲሁም የሕገ-መንግሥት ትርጉምና ውሳኔ አፈጻጸም ክትትል ቋሚ ኮሚቴዎችን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት መርምሮና ተወያይቶ አጽድቋል። የምክር ቤቱ አባላት ቋሚ ኮሚቴዎቹ ባቀረቡት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቶች ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን ያቀረቡ ሲሆን፣ የኮሚቴዎቹ አመራሮችም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር የቀረቡት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቶች እንዲጸድቁ ለድምፅ ያቀረቡ ሲሆን፣ ምክር ቤቱም በሙሉ ድምፅ አጽድቋቸዋል።
በአስተዳደሩ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተቀናጀ መንገድ በመፍታት በኩል ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል
Jul 6, 2026 397
ድሬዳዋ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ አስተዳደር የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በተቀናጀ አሰራር በመመለስ በኩል ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር አስታወቁ። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ ዓመት 12ኛ መደበኛ ጉባዔውን እያካሄደ ነው። ከንቲባ ከድር ጁሃር የአስተዳደሩን የአስፈፃሚና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የ2018 በጀት አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለምክር ቤቱ እያቀረቡ ይገኛሉ። በሪፖርታቸው እንደገለፁትም፤ የአስተዳደሩን ነዋሪዎች መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተቀናጀ መንገድ ለመፍታት በትኩረት ተሰርቷል። ዘንድሮን ጨምሮ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራት እነዚህን ጥያቄዎች ከመመለስ አኳያ ተጨባጭ ውጤቶች የተገኙባቸው መሆናቸውን አንስተዋል። በተለይ ህብረተሰቡን ወደ አምራችነት ለማሸጋገር የተከናወኑ የመሠረተ ልማት አውታሮች፣ የአነስተኛ መስኖና የውሃ ፕሮጀክቶች የገጠሩን ህብረተሰብ ጥያቄዎች በተጨባጭ የመለሱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል እየተሰጡ የሚገኙ ፈጣን አገልግሎቶች የዘመናት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መፍታት ማስቻላቸውንም ነው የተናገሩት። በኮሪደር ልማት የተከናወኑት የተቀናጁ ልማቶችም ከተማዋን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል ነው ያሉት። ባለፉት ዓመታት በኢንቨስትመት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የከተማዋን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከልነት እያረጋገጡ መሆናቸውንም አንስተው እነዚህን ውጤታማና ተጨባጭ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማድረሱ ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ ዓመት 12ኛ መደበኛ ጉባዔው ከንቲባው ባቀረቡት የዕቅድ አፈፃፀም ላይ ተወያይቶ ሪፖርቱን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል። ለሁለት ቀናት የሚካሄደው ጉባዔው ከሪፖርቱ በተጨማሪ ለምክር ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማትን የዕቅድ አፈፃፃምና የድሬዳዋ አስተዳደር የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።
ባገኘነው ዕውቀት ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በመጠቀም ሀገራችንን ለማገልገል ተዘጋጅተናል
Jul 5, 2026 1102
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 28 /2018(ኢዜአ) ፦ያገኘነው ዕውቀት ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በተሻለ መንገድ እንድንረዳው አድርጎናል፤ ይህን ተጠቅመን ሀገራችንን ለማገልገል ተዘጋጅተናል ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ተመራቂዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተመራቂዎች አስመርቋል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመራቂዎች እንደገለጹት፤ በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ የተሰጣቸው ሥልጠና ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል የኢፌዴሪ አየር ኃይል የ3ኛ አየር ምደብ ምክትል አዛዥ እና የተዋጊ ሄሊኮፕተር አብራሪና አስተማሪ ኮሎኔል ደረስ እንዳለ እንደገለጹት፤ በኮሌጁ ያካበቱት እውቀት ሀገሪቱ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን በግልጽ ለመረዳትና ለመተንተን የሚያስችል ከፍተኛ አቅም ፈጥሮላቸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ የምትገኝበት የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን ተለዋዋጭ ሁኔታ በውል ለመረዳት ማስቻሉን ገልጸው፤ ይህንን ስትራቴጂካዊ ዕይታ መሠረት በማድረግ ሀገራቸው የምትሰንቀውን ታላቅ ህልምና ግብ ለማሳካት በቁርጠኝነት ለመስራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል። ሌላው አስተያየታቸውን የሰጡት ከመከላከያ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ሌተናል ኮሎኔል ዶክተር ቴዎድሮስ ገብረ ሩፋኤል በበኩላቸው፤ በስትራቴጂክና ደኅንነት ጉዳዮች ላይ የተከታተሉት ትምህርት ዘርፈ-ብዙ ሁኔታዎችን በጥልቀት ለመተንተን ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የበዙበት መሆኑን አመልክተው፤ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በትብብር መንፈስ የሚንቀሳቀሱ ከሆነ የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ በጎ ውጤት እንደሚያስገኙ አመልክተዋል። ሌላው ሰልጣኝ ከአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የመጡት አቶ ጌታሰው ደሴ እንዳሉት፤ ሥልጠናው ለሀገር አንድነት፣ ለሀገር ፋይዳ እና ለተቋማት ግንባታ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አስተዋጽኦ ለማበርከት ትልቅ አቅምና ወደፊት ለሚሰማሩበት የሥራ መስክም ስንቅ እንደሆናቸው ገልጸዋል። በተመሳሳይ ከልዩ ዘመቻዎች እዝ የመጡት ሌተናል ኮሎኔል ደረጀ ዳባሳ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ያገኙት ዕውቀት የእለት ተእለት ተግባራቸውና ከሙያቸው ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ስትራቴጂካዊ አካባቢውን፣ ጂኦፖለቲካውን እና አጠቃላይ ሁኔታውን በተገቢው መንገድ ለመረዳት አስችሏቸዋል። ትምህርቱ ለተግባራዊ ስራቸው ጠንካራ መነሻ ከመሆኑም በላይ፣ ባላቸው የረጅም ጊዜ ልምድ ላይ ትልቅ አቅም የገነባ መሆኑንም አክለዋል። የኮሌጁ ሰልጣኝ የሆኑት ኮሎኔል እማምር አያሌው በበኩላቸው፤ ቀጣናዊና የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ በደንብ በመረዳት መተንተን የሚችል ጠንካራ ሰራዊት እየተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም በአስተሳሰብ የበሰለ፣ በስትራቴጂካዊ እውቀት የዳበረና ለማንኛውም ሀገራዊ ግዳጅ ዝግጁ የሆነ ሠራዊት መገንባቱን ጠቁመዋል፡፡
ማህበራዊ
የአንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ
Jul 6, 2026 139
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የአንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት ተፈጽሟል። በኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ያሳረፈችው የአንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ሥርዓተ ቀብር፤ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ ወዳጅ ዘመዶቿና በርካታ የሙያ አድናቂዎቿ በተገኙበት በደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል። ከያኒዋ ካበረከተቻቸው በርካታ የሙዚቃ ሥራዎቿ መካከል "ኢትዮጵያ"፣ "አራዳ"፣ "እንደ ኢየሩሳሌም"፣ "ትዝታ"፣ "አንቺ ባለድሪ" እና "አየር ኃይላችን" የሚሉት ተጠቃሽ ሲሆኑ፤ እነዚህ ዜማዎች ዛሬም ተወዳጅነታቸው የማይደበዝዝ ድንቅ የጥበብ ሥራዎቿ ናቸው። በኪነ ጥበብ ህይወቷ በርካታ አይረሴ ድንቅ ስራዎችን ለህዝብ በማበርከት ታላቅ ባለውለታ የነበረችው አርቲስቷ፤ የሁለት ወንድና የአራት ሴት ልጆች እናት ነበረች።
28ኛው የዓለም አቀፍ የሐረሪ ባህል እና ስፖርት ፌስቲቫል በአሜሪካዋ ሜምፊስ ከተማ እየተከበረ ነው
Jul 6, 2026 143
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፡- በርካታ የሐረሪ ማኅበረሰብ አባላት መዳረሻ በሆነችው በአሜሪካዋ ሜምፊስ ከተማ፤ 28ኛው ዓለም አቀፍ የሐረሪዎች የባህልና ስፖርት ፌስቲቫል በተለያዩ ማራኪ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ነው። ዓለም አቀፉ የሐረሪዎችን ቀን መከበሩ ባህላችንን ፤ታሪካችንን፤ ቋንቋችንን እና ቅርሶቻችንን በሚገባ በማወቅ ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተገልጿል። በውጪ ሀገራት የሚኖሩ የክልሉ ተወላጅና ዳያስፖራዎችም ከአገራቸው ጋር ያላቸው ትስስርና ተሳትፎ ይበልጥ የሚጎለብቱበት እንዲሁም በኢንቨስትመንትና በማህበራዊ ዘርፎች በንቃት እንዲሳተፉ አድርጓል። በተለይ የፌስቲቫሉ መከበር በተለያዩ የውጭ ሀገራት የሚኖሩ የሐረሪ ብሄረሰብና ወዳጆች አንድ ላይ በመሰባሰብ ይበልጥ ትስስራቸውን የሚጠናክሩበት እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ የአገሪቱን ጥሩ ገጽታ እንደሚገነባ ተመላክቷል። ከዚህ በተጨማሪም የክልሉ ተወላጆች እና ወዳጆች ባላቸው እዉቀትና ልምድ የአገራቸውን መልካም ገፅታ እንዲገነቡ ከማስቻሉም ባሻገር በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን የሚያደርጉትን ድጋፍና ተሳትፎ በማሳደግ ረገድም ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሏል። በአሜሪካ ሜምፊስ ከተማ እየተካሄደ የሚገኝው 28ኛው ዓለም ዓቀፍ የሐረሪ የባህል እና ስፖርት ፌስቲቫል በቀጣይ ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር ከወጣው መርሐ ግብር ለማወቅ ተችሏል። የሐረሪ ባህል እና ስፖርት ፌስቲቫል ከቀናት በፊት በአሜሪካ ሜምፊስ ከተማ የከተማዋ በዓል ሆኖ እንዲከበር የከተማው ምክር ቤት በአዋጅ መደንገጉ ይታወቃል።
የሴቶችና ህጻናትን ደህንነትና ጤና ለማስጠበቅ እየተሰራ ነው- ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር)/
Jul 6, 2026 150
ባህርዳር፣ሰኔ 29 /2018(ኢዜአ)፡- በችግር ውስጥ የሚገኙ ሴቶችንና ህጻናትን ወደ ማእከል በማስገባት ወደ ቀድሞ ሒወታቸው ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር )ገለጹ። በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የሴቶችና ህጻናት ማገገሚያ ማዕከልን ወደ ስራ የማስገባት መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል። የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ማዕከሉ ተጎጂዎችን በመቀበል የጤና፣ የስነ-ልቦና ህክምናና ሌሎች እንክብካቤዎችን በማድረግ ወደ ቀድሞ ሒወታቸው እንዲመለሱ የሚሰራ ነው። በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች በችግር ወስጥ የሚገኙ ሴቶችንና ህጻናትን ወደ ማዕከሉ በማስገባት ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑንም ገልጸዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም የሀይማኖት አባቶች፣ የትምህርት ተቋማትና መላው ህብረተሰብ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ ነው ያሳሰቡት። የማገገሚያ ማዕከሉ በ123 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ ናቸው። በዚህም ከባህር ዳር ከተማ በተጨማሪ ከደቡብ ጎንደር፣ ምስራቅ ፣ ሰሜንና ምእራብ ጎጃም ዞኖችና አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ለሚመጡ ጉዳት የደረሰባቸው ሴቶችና ህፃናት አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን አስረድተዋል። ማዕከሉ በችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን አክሞ እንዲያገግሙ ከማድረግ ባሻገር የሙያ ስልጠና ወስደው የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ በዘላቂነት የሚቋቋሙበትን ሁኔታ እንደሚፈጥር አስረድተዋል። ማእከሉ ለአንድ ዓመት ሕክምና በማድረግ እንዲቋቋሙ የሚሰራ መሆኑንም ነው ያስረዱት። ማዕከሉ የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጣ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደርና ነዋሪዎች ምቹና ሰላማዊ የስራ አካባቢ በመፍጠር ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል ። አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይም ውይይት ተካሂዷል።
በክልሉ የሕጻናትን መብትና ደህንነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎችን ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ሥራን ማጠናከር ይገባል
Jul 6, 2026 184
አዳማ፣ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ):-በክልሉ የሕጻናት መብትና ደህንነትን በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማጠናከር ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ሥራቸውን ማሳደግ እንዳለባቸው ተገለጸ። የአፍሪካ ሕፃናት ቀን በክልል ደረጃ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ገዛሊ አባሲመልን ጨምሮ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎችና አመራሮች በተገኙበት ዛሬ በአዳማ ከተማ ተከብሯል። የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ገዛሊ አበሲመል እንዳሉት፤ ዛሬ በሕጻናት ላይ የሚሰራው ኢንቨስትመንት ነገ ሰላሟ የተረጋጋና የለማች ሀገር እውን ለማድረግ መሰረት ነው። በመሆኑም በክልሉ የሕፃናትን መብትነና ደህንነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ ይሄን ለማስቀጠል ባለድርሻ አካላት በቅንጅት የጀመሩትን ሥራ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። በተለይ ለሕጻናት የሚሰጠው ነፃ የህግ አገልግሎትና ጥበቃ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የፍትህ ተቋማት በቅንጅት የሚያከናውኑትን ተግባር ማስቀጠል እንዳለባቸው ተናግረዋል። ሕጻናት ለአደጋ ያላቸውን ተጋላጭነት ለመቀነስ የዕለት ተዕለት እገዛና ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል። በክልሉ መንግሥት የተጀመሩ የሕፃናት መዝናኛ ማዕከላት፣ መዋያ እና ማቆያዎች ልማት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት አቶ ገዛሊ፣ ሕጻናት ተገቢውን እንክብካቤና ጥበቃ አግኝተው በስነ ምግባር እንዲያድጉ በጋራ መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። በጨፌ ኦሮሚያ የሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ መስታወት ፈይሳ በበኩላቸው እንዳሉት፤ የሕፃናት ደህንነትና መብትን ለማስጠበቅ፣ ወደትምህርት ቤት ለማምጣትና ፍላጎታቸውን ለማሟላት በትብብር መስራት ይገባል። ሕጻናትን በስነ-ልቦና ለመገንባትና በስነ-ምግባር ለማነፅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲረባረቡም ጥሪ አቅርበዋል። የኦሮሚያ ክልል ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ በበኩላቸው እንዳሉት የሕፃናት ደህንነትና መብትን ለማረጋገጥ የክልሉ መንግሥት በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነፅ ማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ህጻናት ወደትምህርት ቤት እንዲመጡ ከማድረግ ባለፈ እነሱን የሚጎዱ ጎጂ ልማዳዊ ደርጊቶችን ለማስወገድ በትብብር ይሰራል ሲሉም አስታውቀዋል። በብልጽግና ፓርቲ የአዳማ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አጀማ እንደገለጹት፤ ተተኪው ትውልድ በትምህርትና በቴክኖሎጂ ብቁ እንዲሆን ባለፉት የለውጥ ዓመታት ተጨባጭ ሥራዎች ተሰርተዋል። ለእዚህም በከተማዋ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶችን ለማስፋፋት የተሰራውን ሥራ በማሳያነት ጠቅሰዋል። የኦሮሚያ ሕጻናት ፓርላማ ፕሬዚዳንት ተማሪ ሐያት ሙሐመድ በበኩሏ፤ የሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ እንዲቆምና ለትምህርት የደረሱ ሕጻናት መማር እንዲችሉ በክልሉ መንግሥት እየተሰራ ባለው ሥራ የሚበረታታ መሆኑን ተናግራለች። ይሁን እንጂ የሕጻናት ጉዳትና ተጋላጭነትን ለመቀነስ አሁንም በትኩረት መሰራት እንዳለበት ገልጻ፣ በየደረጃው የሚገኙ የሕፃናት ፓርላማዎችን ማጠናከር ያስፈልጋል ብላለች።
ኢኮኖሚ
ጥናቱ በየአካባቢው ያሉ የአምራች ኢንዱስትሪ እምቅ ጸጋዎችን በማወቅና በማልማት የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር ነው
Jul 6, 2026 57
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፡- የብሔራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት በየአካባቢው ያሉ የአምራች ኢንዱስትሪ እምቅ ጸጋዎችን በማወቅና በማልማት የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ገለጹ። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የብሔራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ትግበራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሂዷል። በመድረኩ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል፤ ለሀገራት ልዕልና መለኪያው የማምረቻው ዘርፍ የደረሰበት ደረጃ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያም ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ በመሠራቱ ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረቻው ዘርፍ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን አንስተውም፤ ዘርፉ ለሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ዕድገት ያለው ድርሻ ማደጉን፣ ገቢ ምርቶችን የመተካት ሂደት መሻሻሉንና የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ማደጉን ጠቅሰዋል። የብሔራዊ አምራች ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት በሀገር አቀፍ ደረጃ በየአካባቢው የሚገኙ እምቅ ሀብቶችን፣ መሠረተ ልማቶችንና ሌሎች ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎችን የተሟላ መረጃ የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል። ይህ የተሟላ መረጃ ደግሞ በእውቀት ላይ የተመሠረተ የአምራች ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት። ጥናቱ ወደፊት ለሚከናወኑ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ትክክለኛውን አቅጣጫ የሚያመላክት ከመሆኑ በላይ፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በስፋት ለመሳብ ከፍተኛ ፋይዳ አለው ብለዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የማምረቻ ዘርፉን ለማሳደግ፣ የኑሮ ውድነት ጫናን በዘላቂነት ለመቀነስና ፈጣን የኢኮኖሚ እድገትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ የተሳተፉ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ጥናቱ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሀብቶችን ለማልማት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በጥናቱ የተመለከቱ በየአካባቢው ያሉ እድሎችን ወደ ተጨባጭ ውጤቶች መቀየር የሚያስችሉ የጋራ ሥራዎች ወሳኝ መሆናቸውን አንስተዋል። ለትግበራው ስኬታማነት ሀገር አቀፍ መረጃዎችን ከሚያሰባስቡ ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የቅንጅት ስራዎች መጠናከር እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጥናቱ ለአምራች ኢንዱስትሪው ግብዓት የሆኑትን የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች እምቅ አቅም ለመጠቀም የሀብት ልየታ መደረጉን አድንቀዋል። በአስቻይ ሁኔታም የሰው ኃይልና መሠረተ ልማትን ታሳቢ ማድረጉ ጥሩ መሆኑን አንስተው፥ ሆኖም በየጊዜው ከሚቀያየሩ ሁኔታዎች ጋር የሚጣጣም እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የማምረቻው ዘርፍ በመደመር እይታ ከፍ ያለ ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ፥ ጥናቱ የአምራች ዘርፍ ጸጋዎችን በማወቅና በመጠቀም ብልፅግናን ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል። ጥናቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉንን ሀብቶች መረጃ በአንድ ማዕከል በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ ማካተቱ ለማምረቻው ዘርፍ ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል። ጥናቱን እንደ መነሻ በመውሰድ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ መረጃዎችን በማካተት በክልሉ ለመተግበር ቁርጠኛ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በጥናቱ ሁሉን አቀፍ መረጃዎች መካተታቸው ለማምረቻው ዘርፍ ማደግ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ለባለሀብቶች በእውቀት ላይ የተመሠረተ የኢንቨስትመንት ውሳኔ ለመወሰንና ለቀጣይ የአምራች ዘርፍ ሥራዎች የተሻለ አቅም እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል። የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ፥ በሁሉም አካባቢዎች ያሉትን ሀብቶች በማካተት ተደራሽነቱን በየጊዜው እያሳደገ እንዲሄድ ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት። የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ጥናቱ በሁሉም አካባቢዎች ያለውን ተጨባጭ መረጃ ለማወቅ፣ ዘርፉ ለሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ያለውን ድርሻ ለማሳደግ፣ የምርት ግብዓትና ውጤትን ትስስር ለማጠናከር ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።
በጎንደር ከተማ ገጠር ቀበሌዎች የተጀመረው የሞዴል አርሶ አደሮች መንደር ግንባታ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jul 6, 2026 152
ጎንደር፤ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፡-በጎንደር ከተማ ገጠር ቀበሌዎች የተጀመረው ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር ግንባታ በአዲሱ በጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የከተማው አስተዳደር አስታወቀ፡፡ ከተማ አስተዳደሩ በ2019 በጀት ዓመት አሻጋሪ የእድገትና የዘላቂ የልማት እቅድ ዙሪያ ከአጋር አካላት ጋር የትውውቅ መድረክ ዛሬ አካሂዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ፕላንና ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ፋሲል አብዩ እንደተናገሩት የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ ሁለንተናዊ አገልግሎትን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት መሰረተ ልማትን በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ እና የግብርናውን ኢኮኖሚ ለማዘመንም ፋይዳው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል። በቅርቡ በጎንደር ከተማ በሳይ እና በሳቢያ የገጠር ቀበሌዎች በገጠር ኮሪደር የተገነባውን ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር በአዲሱ በጀት ዓመትም በሌሎች ቀበሌዎች ለማስፋት የቅድመ ዝግጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በአስተዳደሩ ስር በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች 20 ሞዴል የገጠር መንደሮችን ለመገንባት ዝግጅት መጀመሩንም አቶ ፋሲል ጠቅስዋል። የሚገነቡት ሞዴል መንደሮች የኤሌክትሪክ ሃይል፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ፣ መንገድና ዘመናዊ ቤቶችን የሚያካትቱ ሲሆን፣ የግንባታ ቦታ መለየትን ጨምሮ ሀብት የማፈላለግ ሥራዎችን ለማከናወን እየተሰራ ይገኛል። የሞዴል መንደሮቹ ግንባታ ለበርካታ የአካባቢው ወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸው፣ የአርሶ አደሮችንም የሥራ ባህል በመቀየር በኩል ጉልህ አስተዋጾ ያደርጋል ብለዋል። ሞዴል መንደሮቹ አርሶ አደሩ መሰረታዊ የመንግስት አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኝ ያስችሉታል ያሉት ደግሞ፣ የከተማ አስተዳደሩ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ነጻነት መንግስቴ ናቸው፡፡ መምሪያው በሞዴል መንደሮቹ ፣መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በቅርበት ለመፍታት እንደሚሰራም አመልክተዋል። በመድረኩ ላይ የጎንደር ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋ መኮንን፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ ደብሬ የኋላ እና የክፍለ ከተማ የሥራ ኃላፊዎችም ተገኝተዋል።
በከተማዋ በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የታማኝ ግብር ከፋዮች ሚና የጎላ ነው- ከንቲባ ጥራቱ በየነ
Jul 6, 2026 122
ሀዋሳ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፦ በሀዋሳ ከተማ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የታማኝ ግብር ከፋዮች ሚና የጎላ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለፁ። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2017/18 ግብር ዘመን ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የዕውቅናና ሽልማት እንዲሁም የ2018/19 ግብር ዘመን የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በከተማዋ ከግብር ከፋዮች በሚሰበሰብ ገቢ የነዋሪዎችን ፍላጎት የሚያሟሉ ለትውልድ የሚሻገሩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። ታማኝ ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር በአግባቡ በመክፈል በከተማዋ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከንቲባ ጥራቱ አክለውም የከተማዋ ግብር ከፋዮች ከመደበኛ የግብር ግዴታቸው ባሻገር በከተማዋ ለሚከናወነው የኮሪደርና ሐይቅ ዳርቻ ልማት ድጋፍ በማድረግም አሻራቸውን እያኖሩ እንደሚገኙ አውስተዋል። በከተማዋ የሚገኙ ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በሚከናወነው የቀጣዩ ግብር ዘመን ገቢ አሰባሰብ ላይም ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መልኩ ማርቆስ በበኩላቸው በከተማዋ ገቢን አሟጦ ከመሰብሰብ አኳያ የነበሩ ክፍተቶችን በመሙላት በየዓመቱ እያደገ የሚሄድ መሻሻል እየተመዘገበ መሆኑን ገልፀዋል። በ2017/18 ግብር ዘመን 6 ነጥብ 4 ቢሊዮብ ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከእቅድ በላይ 7 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን አመልክተዋል ። ለዚህ ስኬት የሚጠበቅባቸውን ግዴታ በወቅቱና በአግባቡ የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች የጎላ ድርሻ መወጣታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የስነ ስርአቱ ዓላማ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮችን ለማበረታታትና ሌሎችም የነርሱን አርአያ እንዲከተሉ መነሳሳት ለመፍጠር መሆኑን ጠቁመዋል። ዕውቅናና ሽልማት ከተበረከተላቸው ግብር ከፋዮች መካከል በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ተስፋዬ ፀጋዬ በተሰጣቸው ዕውቅናና ሽልማት መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡ በቀጣይ ጊዜያት በላቀ ደረጃ በታማኝነትና በወቅቱ ግብራቸውን በመክፈል በከተማዋ በሚከናወነው የልማት ሥራ ላይ የላቀ አስተዋፅዖ ለማድረግ ያነሳሳቸው መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ላይ የተሰማሩት አቶ አብርሃም ኮላቶ በበኩላቸው ከግብር ከፋዮች በሚሰበሰብ ገቢ ለትውልድ የሚሸጋገሩ መሰረተ ልማቶች የሚገነቡ በመሆኑ በግብር ከፋይነታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በስነ ስርአቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩና የክፍለ ከተሞች የሥራ ኃላፊዎች፣ ግብር ከፋዮችና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
በክልሉ በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jul 6, 2026 131
ቦንጋ፤ ሰኔ29/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። በክልሉ በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል የማሳ፣ የግብዓትና መሰል ዝግጅቶች መደረጋቸውም ተመላክቷል። የክልሉን ያለፈው ዓመት የመኸር አርሻ አፈጻጸም ለመገምገምና የዘንድሮውን የመኸር ግብርና በማስመልከት የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በመድረኩ እንደገለጹት፣ በክልሉ የመኸር እርሻን ስኬታማ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶች በተቀናጀ መልኩ ተጠናክረው ይቀጥላሉ። በየደረጃው ለአርሶ አደሩ የሚደረገውን ድጋፍና ክትትል በማጠናከርና የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። ለመኸር እርሻው ምርጥ ዘር እና የአፈር ማዳበሪያ በበቂ ሁኔታ መቅረቡን አቶ ማስረሻ ጠቁመው፣ በልማቱ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ድጋፍና ክትትሉ መጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። እንደኃላፊው ገለጻ በክልሉ በመኸር ወቅት ከ463ሺህ ሄክታር ማሳ በአዝርት፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት የሚሸፈን ሲሆን ከልማቱም ከ20 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል። በክልሉ የተለያዩ ዞኖች የግብርና መምሪያ ሃላፊዎችም በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለግብርና ቴክኖሎጂ ፣ለማሳ ዝግጅትና ለግብአት አቅርቦትና አጠቃቀም ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ከሀላፊዎቹ መካከል የዳውሮ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ሕብረት ሥራ መምሪያ ሀላፊ ረዳት ፕሮፌሰር በተላ በየነ እንደገለጹት፣ የመኸር እርሻን ስኬታማ ለማድረግ የአርሶ አደሩን የግብርና ግብአት አጠቃቀም ከማሻሻል በተጨማሪ የድጋፍና ክትትል ሥራው ይጠናከራል። በዞኑ ከ90ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመኸሩ ለማልማት መታቀዱን ገልጸው፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ማዳበሪያና ምርጥ ዘርን ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ገልጸዋል። ከማሳ ዝግጅት ጀምሮ በግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ የድጋፍና ክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስታውቀዋል። ሜካናይዜሽን እና ኩታ ገጠም እርሻን በማስፋት የተሻለ ምርት ለመሰብሰብ እንደሚሰራ የተናገሩት ደግሞ የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ሕብረት ሥራ መምሪያ ሀላፊ አቶ ገረመው ገብሬ ናቸው። በዞኑ 139 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት 3 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸው፣ የታቀደውን ለማሳካት ግብአት ከማቅረብ ባለፈ የባለሙያዎች ድጋፍና እገዛ ይጠናከራል ብለዋል። የሸካ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ሕብረት ሥራ መምሪያ ሀላፊ አቶ አይምሮ ደሳለኝ በበኩላቸው፣ በዞኑ ዘንድሮ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የማሳ፣ የግብዓትና ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠን አካባቢዎችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት የማስገባት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jul 6, 2026 203
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠን የተለያዩ አካባቢዎችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት የማስገባት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ምጣኔ ሀብታዊ እና ልማታዊ ዕድገት እንዲሁም የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025/2030” ስትራቴጂን ቀጣይነት ባለው መንገድ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሐይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታላይዜሽን እንዲሁም ወደ ስማርት ሲቲነት ለመቀየር በከፍተኛ ግስጋሴ ላይ የምትገኝ መሆኗን ገልጸዋል። መንግሥት ለዲጂታላይዜሽን ጉዞ መሠረት የሆኑ ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ ዜጎች ከቴክኖሎጂው ጋር አብረው መራመድ የሚችሉበትን ዕውቀትና ክህሎት እንዲያገኙ በርካታ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ለአብነትም የኢትዮ-ኮደርስ አምስት ሚሊዮን ዜጎች ስልጠና ሰፊ መድረክ መመቻቸቱን ጠቅሰው ለጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች የሚደገፉበት ምቹ መደላድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል፡፡ የተለያዩ ተቋማት የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውን በማስፋት የመንግሥት አገልግሎቶችን፣ የንግድ ሥርዓቶችን እና የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ እንዲያዘምኑ መንገድ መከፈቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት መዘርጋት ሀገሪቱ ወደ ስማርት ከተማነት ለምታደርገው ግስጋሴ ስኬት ወሳኝ በመሆኑ፤ ኢንስቲትዩቱ በትኩረት ሲሠራበት መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ ወደ 40 የሚጠጉ አከባቢዎች ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት ማስገባት የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡ እስከ 2018 ዓ.ም ድረስ በሀገሪቱ የሚገኙ ዘጠኝ ከተሞችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ለማስገባት የሚያስችሉ መረጃዎች መሰብሰባቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህም ውስጥ በተለያዩ ከተሞች የተገነቡ የዲጂታል አድራሻ ሥርዓቶች ቀድመው ወደ አገልግሎት ገብተዋል። የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት መዘርጋቱ ዜጎች በቴክኖሎጂ የተደገፉና ዘመኑን የዋጁ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በመሆኑም የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ይበልጥ ለማፋጠን፣ የተለያዩ አካባቢዎችን ወደዚህ ዘመናዊ አድራሻ ሥርዓት የማስገባቱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡
በክልሉ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን ክህሎት በማሳደግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ አግዟል
Jul 6, 2026 199
ሆሳዕና፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን ክህሎት በማሳደግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ማገዙን የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ሀላፊ ሰላሙ አማዶ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ የ5 ሚሊየን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የቴክኖሎጂ ክህሎትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያስቻለ ነው። ወጣቶቹም በስልጠናው ራሳቸውን በማብቃት ከሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ካሉ ካምፓኒዎች ጋር ተቀናጅተው በመስራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ ገቢያቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን አስረድተዋል። በስልጠናው የብቃት ማረጋገጫ ያገኙ ወጣቶችን ከገበያው ጋር በማስተሳሰር ተጠቃሚ መሆናቸውንም አንስተዋል። በሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው ወደ ሥራ ከተቀላቀሉ ወጣቶች መካከል ጫኪሶ ወልዴ አንዱ ሲሆን በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ያገኘው እውቀት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንደሚያደርገው ተናግሯል። ይህም ከሥራ ጠባቂነት ይልቅ የራሱን ስራ በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ አቅሙን እንሚያጠናክርለት ገልጿል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ለዲጂታል ቴክኖሎጂ የተሰጠው ትኩረት የወጣቶችን ሥራ ፈጣሪነትና ተወዳዳሪነት በማረጋገጡ ሌሎችም የእሱን ተሞክሮ እንዲወስዱ መክሯል። ሌላኛው ወጣት አብይ ላቀው በበኩሉ በኢትዮ ኮደርስ መርሃ ግብር የወሰደው ስልጠና በዘርፉ የነበረውን እውቀት ይበልጥ ለማሳደግ እንዳስቻለው ተናግሯል። ስልጠናው በኦን ላይን ገቢ በማመንጨት ተጠቃሚ መሆን የሚያስችለውን በቂ እውቀት ለማግኘት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረለትም ጠቁሟል። በዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚሰሩ ሥራዎችን በቤቱ ሆኖ በኦን ላይን በመስራት ገቢ ማግኘት መጀመሩን ነው የገለጸው። ባለፉት ሁለት ዓመታት በክልሉ ከ242ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን ተከታትለው የእውቅና የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት፤ ይበልጥ ተደራሽና ቀልጣፋ በመሆን የደንበኞችን እርካታ ያረጋግጣል
Jul 3, 2026 1079
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት፤ የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ተደራሽና ቀልጣፋ በማድረግ የደንበኞችን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ የሚያረጋግጥ መሆኑን የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎችና ባለሙያዎች ገለጹ። አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ተደራሽ እና ጥራት ያለው ለማድረግ የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ ለማኅበረሰቡ ይበልጥ ተደራሽ በመሆን ወደ አገልግሎት የገቡት ሁለት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ ባሶች ቴክኖሎጂዎቻቸው ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት የሰጡ ናቸው፡፡ በዚህም አንደኛው ባስ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ (EV) የሚሠራ ሲሆን ሁለተኛው የተፈጥሮ ጋዝን በመጠቀም የሚንቀሳቀስና አገልግሎት የሚሰጥ ነው፡፡ እነዚህ ተንቀሳቃሽ መስኮቶች የስድስት ቁልፍ የፌዴራል ተቋማትን አገልግሎቶች የሚሰጡ ሲሆን፣ አገልግሎቶቹም ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ በመሄድ የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው፡፡ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተጠቃሚዎች እንደገለጹት፤ ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት እጅግ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገኟቸው ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ አቶ በኃይሉ ወርቁ በሰጡት አስተያየትም ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት ማኅበረሰቡ ባለበት ቦታ ሆኖ ፈጣንና የተቀላጠፈ የመንግሥት አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉን ገልጸዋል። ይህ የዲጂታል ትግበራ አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ ከሙስና የጸዳ፣ ግልጽና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑንም አክለዋል። አቶ አስቻለው ጓዴ በበኩላቸው ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት በየአካባቢው እየተዘዋወረ አገልግሎት መስጠቱ ማኅበረሰቡን ከተጨማሪ ወጪና ከተንዛዛ እንግልት እንደታደጋቸው ገልጸዋል። አሠራሩ ጊዜና ገንዘብን በአግባቡ ለመቆጠብ ያስቻለ በመሆኑም የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል፡፡ በወረፋና በተለያዩ ቦታዎች መጉላላት ሳይኖር፣ በአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን ማግኘት መቻሉ ጊዜንና ጉልበትን በከፍተኛ ደረጃ እየቆጠበላቸው መሆኑን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ወርቅነሽ እሸቱ ናቸው፡፡ የአገልግሎቱ ዲጂታላይዝ መሆን ከተገልጋዩ ባሻገር ለባለሙያዎችም የላቀ የሥራ ተነሳሽነትና ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠሩን አገልግሎቱን የሚሰጡ ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡ የአገልግሎቱ ባለሙያ አቶ አሰግድ ንዋይ እንደገለጹት፣ አዲሱ አሠራር ተቋማትና ባለሙያዎች ወደ ተገልጋዩ ይበልጥ እንዲቀራረቡና ግልጽነት የሰፈነበት አገልግሎት እንዲሰጡ አስችሏል። እሌኒ ውድነህ በበኩሏ፤ አዲሱ የዲጂታል አሠራር ለሠራተኞች ጤናማ የሥራ ድባብ ከመፍጠሩም በላይ፣ የተገልጋዮች እርካታ ለባለሙያው ትልቅ መነሳሳት መሆኑን ጠቁማ፣ ተንቀሳቃሽ መሶብ ማኅበረሰቡን በእጅጉ ማስደሰቱን ገልጻለች። የፌደራል መሶብ አገልግሎት ማዕከል ምክትል ኦፕሬሽናል ዘርፍ ኃላፊ ቤዛዊት ብርሃኔ በበኩላቸው፤ ይህ ዘመናዊ አሠራር ኅብረተሰቡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሁልጊዜም በታላቅ እምነት፣ ምቾትና አስተማማኝ በሆነ መልኩ እንዲያገኝ በር የከፈተ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል
Jul 1, 2026 1726
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻሉን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ አገልግሎቱ በተጀመረ አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ3ሺህ 600 በላይ ነዋሪዎች የዲጂታል አገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከትውልድ እስከ ሞት ያሉ ወሳኝ ኩነቶችን የሚመዘግብ ተቋም ነው፡፡ ይህንን የአገልግሎት አሰጣጡን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ሰፊ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፣ በቅርቡም አዲሱን ዲጂታል ስርዓት በስኬት አስመርቆ ስራ አስጀምሯል። ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር ነዋሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ወይም በኮምፒውተራቸው አማካኝነት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ምቹ አሰራር የፈጠረ ነው። በኦንላይን የተጀመሩት አራቱ ዋና ዋና አገልግሎቶችም መታወቂያን ከፋይዳ መረጃ ጋር ማስተሳሰር፣ የነዋሪነት መታወቂያ እድሳትና የጠፋን መተካት፣ ያላገባ የምስክር ወረቀት አገልግሎት እና የልደት ምስክርነት ወረቀት አገልግሎት ናቸው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ፤አዲሱ የዲጂታል አሰራር ጊዜን በመቆጠብ፣ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ትልቅ ጠቀሜታ እያገኙበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። ከተጠቃሚዎች መካከል የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ነዋሪ አቶ አባትዬ ተስፋዬ ፤ አገልግሎቱን በቀላሉ ከቤታቸው ሆነው በቴክኖሎጂው አማካኝነት ማጠናቀቃቸውን ገልጸው፣ የተዘጋጀላቸውን መታወቂያ ለመረከብ ብቻ ወደ ወረዳው መምጣታቸውን ተናግረዋል። ይህ አሰራር ጊዜን ከመቆጠቡ ባለፈ፣ ዘመናዊና ስልጡን አሰራር በመሆኑ ከፍተኛ እርካታ እንደፈጠረላቸውም ጨምረው አስታውቀዋል። ሌላኛው የዚሁ ወረዳ ነዋሪና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ኢሳያስ ግርማ በበኩላቸው፤ የዲጂታል አሰራሩ ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ በዘርፉ ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ አንጻር አይነተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ ሆነው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ወይም በኮምፒውተራቸው አስፈላጊውን ሰነድ አያይዘው ካመለከቱ በኋላ የሚፈልጉት አገልግሎት በፍጥነት እየተሰጣቸው ይገኛል ያሉት ደግሞ በኤጀንሲው የኦንላይን አገልግሎት ባለሙያ የሆኑት ደሳለኝ ዘርጋ ናቸው። ተገልጋዩ ወደ ወረዳ በአካል የሚመጣው የተዘጋጀውን ሰርተፊኬት ወይም መታወቂያ ለመውሰድ ብቻ መሆኑን ባለሙያው አብራርተዋል። ሌላኛዋ የኤጀንሲው የኦንላይን አገልግሎት ባለሙያ ሶስና አወል በበኩላቸው ፤ይህ አሰራር ቀደም ሲል በወረዳዎች ላይ ይፈጠር የነበረውን ከፍተኛ የህዝብ ግርግርና የአገልግሎት አሰጣጥ ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰው ይገኛል ብለዋል። ይህም ሰራተኞች በተረጋጋ መንፈስና በነጻነት ስራቸውን በጥራት እንዲያከናውኑ ትልቅ እገዛ ማድረጉን አክለዋል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሤ በበኩላቸው፤ አዲሱ የኦንላይን አገልግሎት አሰጣጥ በተቋሙ ይስተዋሉ የነበሩ የአገልግሎት መቆራረጦችንና የተገልጋይ እንግልትን በከፍተኛ ደረጃ እየቀረፈ መሆኑን አስታውቀዋል። አገልግሎቱ በተጀመረ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ3ሺህ 600 በላይ ነዋሪዎች ከቤታቸው ሆነው በቴክኖሎጂው መጠቀም መቻላቸውን ለአብነት አንስተዋል። የኦንላይን አገልግሎቱ በተገልጋይና በአገልግሎት ሰጪዎች መካከል ያለውን ቀጥተኛ ንክኪ በማስቀረት ብልሹ አሰራርን በጽኑ የሚከላከል መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂንና ስማርት ከተማ የመፍጠር ግብን የሚያሳካ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
ስፖርት
ፖርቹጋል ከስፔን : ተጠባቂው የጥሎ ማለፍ ፍልሚያ
Jul 6, 2026 422
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፡- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ የሚገቡ ሀገራት የሚለዩባቸው ሁለት ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ። ምሽት አራት ሰዓት ፖርቹጋል ከስፔን በዳላስ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል። ፖርቹጋል በ32ቱ የጥሎ ማለፍ ዙር ክሮሺያን 2 ለ 1 ስታሸንፍ ስፔን በበኩሏ ኦስትሪያን በመርታት ቀጣዩን ዙር ተቀላቅላለች። የአውሮፓ እግር ኳስ ኃያላኑ በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2010 ባዘጋጀችው 19ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በተመሳሳይ 16 ውስጥ ተገናኝተው ስፔን በዴቪድ ቪያ ጎል 1 ለ 0 ማሸነፏ ይታወሳል። በወቅቱ ስፔን የዓለም ዋንጫው ባለቤት መሆን የቻለች ሲሆን፣ ይህ ስኬትም እስካሁን ድረስ በታሪኳ ያስመዘገበችው ብቸኛ የዓለም ዋንጫ ድሏ ነው። በሩሲያ እ.አ.አ በ2018 በተካሄደው 21ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በምድብ ሁለት ተገናኝተው ሶስት አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ሲሆን በወቅቱ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለፖርቹጋል ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ብሔራዊ ቡድኖቹ ከዚህ ቀደም እርስ በእርስ ባደረጓቸው 41 ጨዋታዎች ስፔን 17 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ስትይዝ ፖርቹጋል ብስድስቱ ድል ሲቀናት በቀሪ 18 ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። በዛሬው ጨዋታ የ41 ዓመቱ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና የ18 ዓመቱ ላሚን ያማል የሚጠበቁ ሲሆን በጨዋታው ተመጣጣኝ እና አዝናኝ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ በሩብ ፍጻሜው ከአሜሪካ እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ይገናኛል። አሜሪካ ከቤልጂየም ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት በሲያትል ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ከዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው አሜሪካ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ቦሲኒያ ሄርዞጎቪናን 2 ለ 0 ማሸነፏ እንዲሁም ተጋጣሚዋ ቤልጂየም በበኩሏ ሴኔጋልን ከ2 ለ 0 መመራት ተነስታ ውጤቱን ቀልብሳ 3 ለ 2 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር መቀላቀሏ ይታወቃል። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም በዓለም ዋንጫው ሁለት ጊዜ ተገናኝተዋል። ኡራጓይ እ.አ.አ በ1930 ባዘጋጀችው የመጀመሪያ የፊፋ የዓለም ዋንጫ በምድብ አራት ተገናኝተው አሜሪካ 3 ለ 0 አሸንፋለች። በርት ፓቴናውድ ሶስቱንን ግቦች ከመረብ በማሳረፍ በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ሀትሪክ የሰራ ተጫዋች መሆንም ችሏል። ብራዚል እ.አ.አ በ2014 ባዘጋጀችው 20ኛው ፊፋ ዓለም ዋንጫ 16 ውስጥ ተገናኝተው ቤልጂየም 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ አልፋለች። ኬቨን ደ ብሮይን እና ሮሜሎ ሉካኩ ግቦቹን ሲያስቆጥሩ ሁለቱም ተጫዋቾች በአሁኑ የዓለም ዋንጫ የቤልጂየም ስብስብ ውስጥ ይገኛሉ። ጁሊያን ግሪን በወቅቱ የአሜሪካን ብቸኛ ጎል ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ሁለቱ ሀገራት ከ12 ዓመታት በኋላ በድጋሚ 16 ውስጥ ተገናኝተዋል። በአጠቃላይ ሀገራቱ እርስ በእርሳቸው ሰባት ጊዜ ተጫውተው ቤልጂየም ስድስቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ስትይዝ በቀሪው አንድ ጨዋታ (በመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ) አሜሪካ ድል ቀንቷታል። በአሜሪካ በኩል በውድድሩ ሶስት ግቦችን ያስቆጠረው የአሜሪካው ፍሎሪያን ባሎጉን ከቦሲኒያ ጋር በነበረው ጨዋታ የተመለከተው ቀይ ካርድ አግባብ ባለመሆኑ ምክንያት ተነስቶለት በጨዋታው ላይ እንዲጫወት መወሰኑን ፊፋ አስታውቋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋኒቲኖ የቀይ ካርድ ውሳኔው በድጋሚ እንዲታይ ደውለው መጠየቃቸውን ተከትሎ ቀይ ካርዱ መነሳቱ የዓለም አቀፉ እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል ላይ የተአማኒነት ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል። ተጋጣሚዋ ቤልጂየም ውሳኔውን ፍጹም ተቀባይነት የለውም ስትል የተቃወመች ሲሆን የሁሉም ተሳታፊ ሀገራት መብት እንዲጠበቅና በእግር ኳሱ ፍትሃዊነት እንዲሰፍን ሁሉንም አማራጮች እንደምትመለከት አስታውቃለች። ትራምፕ ውሳኔውን ተከትሎ ፊፋን ያመሰገኑ ሲሆን ፍትሃዊነትን ያሰፈነ ውሳኔ ሲሉ መግለጻቸውን ተከትሎ ውሳኔው ከጨዋታው በፊት ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል። ለቤልጂየም በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በዓለም ዋንጫው ያስቆጠሩት ሊአንድሮ ትሮሳርድ እና ሮሜሎ ሉካኩ በጨዋታው የሚጠበቁ ተጫዋቾች ናቸው። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ጨዋታው አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው ይገናኛሉ።
ኖርዌይ እና እንግሊዝ ወደ ሩብ ፍፃሜው ተቀላቀሉ
Jul 6, 2026 273
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር እንግሊዝ እና ኖርዌይ ወደ ሩብ ፍፃሜው ተቀላቅለዋል። ቀደም ብሎ በተደረገው ጨዋታ ኖርዌይ ብራዚልን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ማምሻውን በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አርሊንግ ሃላንድ በ79ኛው እና ደቂቃ 90ኛው ደቂቃ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፏል። የ25 ዓመቱ ሃላንድ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ሰባት አድርሷል። ከአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ እና ከፈረንሳዊው ኪሊያን ምባፔ ጋር ተመሳሳይ የግብ መጠን ማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በጋራ መምራት ችሏል። ለሀገሩ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 62 ከፍ አድርጓል። ኔይማር በ100ኛው ደቂቃ የብራዚልን ብቸኛ ጎል በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል። በሌላ በኩል እንግሊዝ አዘጋጇን ሜክሲኮን 3 ለ 2 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍፃሜው ተቀላቅላለች።በአስር ተጫዋች ሁለተኛውን አጋማሽ የተጫወቱት እንግሊዞች በሀሪ ኬን እና ቤሊንግሀም ሁለት ጎሎች አሸንፈዋል። ሀሪ ኬን በውድድሩ ስድስተኛ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል። ሀሪ ኬን በአለም ዋንጫው በድምሩ ያስቆጠራቸውን የጎሎች መጠን ወደ 14 ከፍ አድርጓል። ኖርዌይ በቀጣይ ዙር እንግሊዝን በሚያሚ ትገጥማለች።
ሲዳማ ቡና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ተረከበ
Jul 5, 2026 681
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦ በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ሀብታሙ በ70ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ጎሉን አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ54 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና በ68 ነጥብ ዓመቱን ጨርሷል። ጨዋታውን ተከትሎ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉ አሸናፊ የሆነው ሲዳማ ቡና ዋንጫውን ተረክቧል። የሊጉ ዋንጫ ሲዳማ ቡና በ1999 ዓ.ም ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ያሳካው ትልቁ ድሉ ነው። ሻምፒዮንነቱን ተከትሎ በቀጣዩ ዓመት ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ይሳተፋል። ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ዋንጫውን ለማንሳት ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ይፋለማል። በዋንጫ ስነ ስርዓቱ ላይ በርካታ የሲዳማ ቡና ደጋፊዎች ታድመዋል። በተጨማሪም ሲዳማ ቡና ዛሬ የተጠናቀቀውን ከ20 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በማጠቃለያ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻን በመለያ ምት በመርታት ዋንጫውን አንስቷል። በዚህም ድርብ ድል አሳክቷል። በሊጉ የመዝጊያ ስነ ስርዓት የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የፕሪሚየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የዘንድሮው የሊጉ ውድድር ዛሬ በ38ኛ ሳምንት ተቋጭቷል። ምድረ ገነት ሽሬ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ መቀሌ 70 እንደርታና አርባምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረዱ ክለቦች ናቸው። ከከፍተኛ ሊግ ያደጉት ሃላባ ከተማ እና ጋሞ ጨንቻ በቀጣዩ የውድድር ዓመት በሊጉ ይሳተፋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ ናትናኤል ዳንኤል እና የፋሲል ከነማው ታምራት እያሱ በተመሳሳይ 15 ጎሎች በጋራ የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን አጠናቀዋል። የሲዳማ ቡናው አቤል ያለው በ14 ግቦች ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል።
ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና የዋንጫ ሽልማቱን በሚረከብበት ዕለት ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ይጫወታል
Jul 5, 2026 443
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጠናቀቃል። ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና በ68 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ51 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ሲዳማ ቡና የሊጉን ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ማንሳቱን ያረጋገጠው በ36ኛ ሳምንት ከነገሌ አርሲ ጋር አንድ አቻ መለያይቱን ተከትሎ ነው። በ1999 ዓ.ም የተመሰረተው ሲዳማ ቡና የፕሪሚየር ሊጉ ዋንጫ ባለቤት መሆኑ በ19 ዓመት የክለቡ ጉዞ ውስጥ ትልቁ የሚባለው ስኬቱ ነው። ለረጅም ሳምንታት የሊጉ አናት ላይ የቆየው እና በአንጻራዊነት ወጥ አቋም ያሳየው ሲዳማ ቡና ከዛሬው ጨዋታ በኋላ ታሪካዊውን ዋንጫ የሚረከብ ይሆናል። የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ የዋንጫ አቀባበል ድባቡን ይበልጥ ለቡድኑ ያደምቀዋል። ቡድኑ ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎም በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት ይሳተፋል። በተጨማሪም ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር የሚፋለም ይሆናል። ዓመቱን በሁለት ዋንጫ የማጠናቀቅ እድል አለው። በ37ኛ ሳምንት ከሃዋሳ ከተማ ጋር አንድ አቻ የተለያየው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ዓመቱን በድል ለመደምደም ከሻምፒዮኑ ጋር ይፋለማል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካሸነፈ አምስተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቅቃል። ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው። ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ፍጻሜውን ያገኛል። በዝናብ ስጋት ምክንያት ከአዲስ አበባ ወደ ሃዋሳ የተዛወረው የሲዳማ ቡና እና የኢትዮ ኤሌክትሪክ የ2018 ዓ.ም የሊጉ መዝጊያ ጨዋታ እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር በሳምንቱ አጋማሽ ማስታወቁ ይታወሳል።
አካባቢ ጥበቃ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ
Jul 6, 2026 202
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፡-የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከ30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ(ኮፕ 30) ፕሬዝዳንት አምባሳደር አንድሬ አራንሃ ኮሪያ ዶ ላጎ እና ከቡድናቸው ጋር ውይይት አድርገዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) አስተናጋጅ ለመሆን በምታደርገው ዝግጅት ላይ፣ ከቀደምት አዘጋጅ ሀገራት ልምድ መቅሰም ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ሆኗል። በዚህም መንፈስ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዝዳንት አምባሳደር አንድሬ አራንሃ ኮሪያ ዶ ላጎ እና ከቡድናቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የውይይቱ ዓላማ ዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ጉባኤ ከማዘጋጀት ጋር የተያያዙ ዕውቀቶችን እና የተወሰዱ ትምህርቶችን መለዋወጥ መሆኑን ተመላክቷል።
በአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን ጠንካራ የዕፅዋት ጤና ጥበቃ ሥርዓት መገንባት ይገባል
Jul 6, 2026 247
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ አህጉር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ውጤታማ የዕፅዋት ጤና ጥበቃ ሥርዓት መገንባት ወሳኝ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። "የእፅዋት ሀብቶችን እና ተቋማትን ለመጠበቅ የአፍሪካ ሀገራትን በሳይንስ እና በዲጂታል መሳሪያዎች ማብቃት" በሚል መሪ ኃሳብ የተዘጋጀው የአፍሪካ ዕፅዋት ጤና ጥበቃ ፕሮግራም የስትራቴጂክ አጋርነት መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ አፍሪካ ግብርናውን ለመለወጥና ዘላቂ ልማት ለማምጣት የምታደርገው ጥረት በድንበር ተሻጋሪ ተባዮች፣ በወራሪ ዝርያዎች፣ በድንገተኛ በሽታዎች እና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ከፍተኛ አደጋ ተደቅኖበታል። እነዚህ ተግዳሮቶች በምርት፣ በብዝሃ ሕይወት እና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ በመሆናቸው፣ በእፅዋት ጤና ላይ መዋዕለ ነዋይ ማፍሰስ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ስኬት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ተባይና የእፅዋት በሽታዎች በድንበር የማይገደቡ በመሆናቸው፣ የትኛዋም ሀገር ተግዳሮቶቹን ብቻዋን መፍታት ስለማይቻል አህጉራዊ የጋራ ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል። ጠንካራ የዕፅዋት ጤና ጥበቃ ሥርዓት መገንባት የግብርና ኢንቨስትመንቶችን ለመጠበቅ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እና የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳርን ለመንከባከብ መሠረታዊ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ደህንነቱ የተጠበቀና ተወዳዳሪ የንግድ ሥርዓትን ለማመቻቸት እንዲሁም የምግብ ሥርዓትን የመቋቋም አቅም ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። በኢትዮጵያም ዘላቂ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማምጣት የዕፅዋትን ጤና የመጠበቅ ተግባር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል። የዓለም አቀፉ የዕፅዋት ጥበቃ ኮንቬንሽን ጸሃፊ ኤንሪኮ ፔሮቲ በበኩላቸው ድርጅቱ ጠንካራ እና የበለጠ የመቋቋም አቅም ያለው የዕፅዋት ጤናን ለመገንባትና የምግብ ዋስትናን ለመደገፍ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ገልጸዋል። አጋርነቶችን ማጠናከርና አዳዲሶችን መፍጠር እንደሚገባ ገልጸው፣ በአፍሪካ የዕፅዋት ጤና ፕሮግራም በኩል የተመዘገበው አስደናቂ እድገት በዓለም አቀፍ ደረጃ የላቀ ተፅዕኖ ለመፍጠር መሠረት መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኢንተር-አፍሪካን የዕፅዋት ጤና ጥበቃ ምክር ቤት አስተባባሪ ሳሊው ኒያሲ (ዶ/ር)፤ ተቋማቸው ለብሔራዊ ተቋማት የክትትል፣ የላቦራቶሪ ምርመራና የመከላከል አቅምን በማሳደግ፤ በሳይንስ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ አሰጣጥንና ቀጣናዊ የመረጃ ልውውጥን እያጠናከረ ይገኛል ብለዋል። ይህ ፕሮግራም የአፍሪካ ህብረትን የዕፅዋት ጤና ስትራቴጂ ትግበራ የሚደግፍ እና በአካታች የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮግራም ስር የተገለጹትን የአጀንዳ እ.አ.አ 2063 ለማሳካት እየተሰሩ ካሉት ስራዎች አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት ጊዜያዊ ተወካይ ኦርላንዶ ሶሳ በበኩላቸው፣ ለስኬቱ የመንግስታት፣ የቀጣናዊ ድርጅቶች፣ የልማት አጋሮች፣ የቴክኒክ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ የተቀናጀ አጋርነት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የገንዘብ ድጋፍ፣ የቴክኒክ እውቀት፣ ስልጠና፣ የምርመራ አገልግሎት፣ የዲጂታል ድጋፍ ጋር የተያያዙ አስተዋፅኦዎች ተቀናጅተው ዘላቂ አቅምን ለመገንባት መዋል እንዳለባቸው ተናግረዋል። ለአርሶ አደሮች እና በዕሴት ሰንሰለቱ ውስጥ ላሉ ተዋናዮች ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያን ስም ከፍ ያደረገ ነው
Jul 6, 2026 222
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ ዐሻራ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያን ስም ከፍ ያደረገ መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራርና ሠራተኞች በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ጎተራ ማሳለጫ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ አከናውነዋል። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሁሉም መስክ ተጨባጭ ሀገራዊ ለውጦች እንዲመዘገቡ መሰረት እየጣለ ነው። የተሸረሸሩ እና የተጎዱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ አስችሏል ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፤ በምግብ ራስን የመቻል ግቦችን በማሳካት ረገድ አዎንታዊ ውጤቶች እየተመዘገበበት ነው ብለዋል። አገልግሎቱ ባለፉት ዓመታት በመርሃ ግብሩ በንቃት መሳተፉን ጠቅሰው፤ በ2018 በጀት ዓመት በአረንጓዴ አሻራ እና በተለያዩ በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያጎሉ ተግባራትን በሰፊው እንደሚያከናውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የወሰደችው የአረንጓዴ ዐሻራ ተግባራዊ ምላሽ ስሟን በዓለም መድረክ ከፍ ማድረጉን አስረድተዋል። ከዚህም ባለፈ ስለ አፍሪካ የሚነሱ የተዛቡ ትርክቶችን በማስተካከል ከፍያለ አህጉራዊ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በአዲስ አበባ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ብርሃኑ አበራ በበኩላቸው፤ አረንጓዴ ዐሻራ የደን ሽፋን እንዲጭምር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። ሁሉም በየአካቢው ችግኞችን በመትከል ሀገራዊ ኃላፊነቱን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የፕላንኒንግ ዳይሬክተር መሳይ አበበ እንደገለጹት፤ ዛሬ የምንተክለው ችግኝ ለቀጣዩ ትውልድ ዋስትና ነው ያሉ ሲሆን፤ ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክቦ ለውጤት ማብቃት ከኛ ይጠበቃል ብለዋል። አሻራዬን በማኖሬ እኮራለሁ ያሉት የአገልግሎቱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር ማስተዋል ገዳ፤ የምንተክለው ችግኝ ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ ተስፋን ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል። በቀጣይም የአረንጓዴ ዐሻራ ዘላቂ ግቦች እንዲሳኩ የሚጠበቅብኝን እወጣለሁ ብለዋል።
ያለፉት ዓመታት የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራዎች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የላቀ አስተዋፅኦ አበርክተዋል
Jul 6, 2026 240
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራዎች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የላቀ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። በከተማ አስተዳደሩ የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በጉሩሞ ላዲሳ ቀበሌ ተካሂዷል። በወቅቱም የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማርያም እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ሥራዎች የማኅበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ ያስቻሉ ናቸው። በመርሃ ግብሩ ከዚህ ቀደም የተከናወኑ ተግባራት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የላቀ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውንም ገልጸዋል። መርሃ ግብሩ የመሬት ለምነት እንዲጠበቅና የውሃ አካላት አቅማቸው እንዲጨምር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመው፣ ይህም በግብርናው ዘርፍ ለውጥ እንዲመጣ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘቱን አስታውቀዋል። ዘንድሮ በሚከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በከተማው የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር የሚጠብቁና ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ አበርክቶ ያላቸው ችግኞች በስፋት እንደሚተከሉ ተናግረዋል። በዚህም ለደን፣ ለጥላ፣ ለውበት፣ ለኢኮኖሚ ምንጭነት የሚውሉ እንደ ቡና፣ ፍራፍሬ እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ላላቸው የችግኝ ዓይነቶች ትኩረት በመስጠት የመትከል ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በሕዝቡ ዘንድ እየዳበረ የመጣው ችግኝ የመትከል ባህል እየተጠናከረ መምጣቱን ጠቁመው፣ የተተከሉትን ችግኞች በመጠበቅና በመንከባከብ ለውጤት እንዲበቁ የሚደረገው የተቀናጀ ጥረት ይጠናከራል ብለዋል። የከተማው ግብርና መምሪያ ኃላፊ ንጋቱ ቡሹራ በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የቡና፣ የእንሰት፣ የፍራፍሬና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተከላ መጀመሩን ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩም 4 ነጥብ 6 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል 680 ሄክታር መሬት ለማልማት መታቀዱን አስታውቀዋል። ችግኝ መትከል ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር መስተካከል የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ በመገንዘብ በየዓመቱ ችግኝ እየተከሉ መሆኑን የሚናገሩት ደግሞ አርሶ አደር ካሳሁን ሎሃ እና አርሶ አደር ኢዮብ ሰማ ናቸው። ችግኝ መትከል ከጀመሩ ወዲህ የተራቆቱ አካባቢዎች ለምተው ምርት መስጠት በመጀመራቸው፣ የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ በተጨማሪ የደረሱ ፍራፍሬዎችን ሸጠው በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። ይህንን ለማስቀጠልም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል ቤተሰቦቻቸውን በማስተባበር ለዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ወደ ሥራ መግባታቸውን አክለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 16676
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 11067
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 9868
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 9767
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jul 5, 2026 554
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018(ኢዜአ):- የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? ኢትዮጵያ እያከናወነች ነው የገጠር ትራንስፎርሜሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት የተጀመረው የከተሞች ኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩም ተስፋፍቶ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗርና አመጋገብ እንዲሁም ጤናን መሰረት በማድረግ የገጠር ኮሪደር ልማት በመከናወን ላይ ይገኛል። ለጤናም ይሁን ለኑሮ ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ለዘመናት በተመሳሳይ ሁኔታ የኖረው አርሶና አርብቶ አደሩ አሁን ላይ መሰረታዊ የአኗኗር ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በገጠር የኮሪደር ልማት የሰዎችና እንስሳት መኖሪያ እየተለየ፤ በባዮ ጋዝ እና በፀሃይ ብርሃን በሚሰራ የሃይል ምንጭ መብራት ማግኘትና ምግብ መስራት የተቻለበት፤ በጓሮ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎችን መመገብ የሚቻልበት ዘመናዊ አኗኗር ጀምረዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን የልማት እንቅስቃሴው በጅምር ላይ ቢሆንም በብዙ አካባቢዎች እየተስፋፋ ሞደል መንደሮች እየተበራከቱ መጥተዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ሀማሳ በ79 ነጥብ 4 ሄክታር መሬት ላይ የተሰራው ሞዴል መንደር የዚሁ ጥረት ማሳያ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቆ ለነዋሪዎች የተላለፈው የሀማሳ ሞዴል መንደር በአንድ ግቢ ውስጥ የንጽህና መጠበቂያ፣ የተደራጀ የቤት እንስሳት ማቆያ፣ በባዮ ጋዝ የሚሰራ የሃይል አቅርቦትን እንዲሁም የተሟላ የጓሮ ግብርናን ማእከል አድርጎ የተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም መንግሥት በተለያዩ የገጠር አካባቢዎች ሞዴል ቤቶችን መስራቱን አስታውሰው ከዚህ በመነሳት ነዋሪዎቹ በራሳቸው ተነሳሽነት የራሳቸውን መኖሪያዎች መገንባት ጀምረዋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው ''ንጽህና ካለ ጤና አለ፤ ምግብ ካለ ጤና አለ፤ የተስተካከለ ኮሪደር ካለ ሰላም አለ። እነዚህ ጉዳዮች ከፍተኛ ግምት ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል። የዜጎቻችንን ሕይወት ይቀይራሉ፤ የአኗኗር ዘዬአችንን ያሻሽላሉ፤ ኢትዮጵያን ወደ ምናስበው ከፍታ ወደ ምናስበው መሻሻል የመውሰድ አቅም አላቸው'' ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ቀጥሎ በጋሞ ዞን የ'ዮ ሆልዲንግ’ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከጥቂት ዓመታት በፊት ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚሆን የድንጋይ ከሰል ከውጭ ሀገር ለማስገባት እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር ውጪ የሚደረግ መሆኑን አንስተዋል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ የተለያዩ የከሰል ማምረቻ ፋብሪካዎች ተመርቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውንና ይህም የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ ለውጭ ገበያ የማቅረብ እድል ይፈጥራል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአርባምንጭ ዘመናዊ የኮንፈረንስ ሪዞርት መርቀው ስራ ያስጀመሩ ሲሆን በዶርዜ ሎጅ እና አካባቢው መሰረተ ልማቶችን እንዲሁም የአርባ ምንጭ ከተማን የኮሪደር ልማት፤ በከተማዋ የሚገኘውን ኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓንም ጎብኝተዋል። በሁሉም ዘርፎች ኢትዮጵያ ማከናወኗን አጠናክራ ቀጥላለች፤ እድገትና ማንሰራራቷ ላይቀለበስ ጉዞውን ቀጥሏል። ከዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች አንዱ የቱሪዝም ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት እንዳስታወቀው የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በዓለማችን ከፍተኛ ተጓዦች ከተመረጡ የዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች መካከል አንዱ ሆኗል። በዩሮኒውስ የዜና አውታር በተደረገ ጥናት፤ ሁሉንም የዓለም ክፍሎች ያዩ አንጋፋ ተጓዦች ካስቀመጧቸው ተወዳጅ የዩኔስኮ የዓለም ቅርሶች መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በግንባር ቀደምትነት ተቀምጧል። በዚሁ ሳምንትም ከአርባ በላይ ሀገራት እና ከአሥር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ዲፕሎማቶች የላሊበላ ከተማና ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። ይህ ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑክ በቆይታው ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን፣ የሕንጻ ጥበብ እና የኢንጂነሪንግ ጥበብ ማስተርፒስ እንዲሁም የሃይማኖትና የታሪክ ሕያው ምስክር የሆኑትን የዓለም ቅርስ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አስተማማኝ መከታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ያሰለጠናቸውን ተመራቂዎች በዚሁ ሳምንት አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ሰራዊቱ የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝ መልኩ እየጠበቀ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ ታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች ግንባር ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያን ከባሕር ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ “ፅምዶ” በሚል የተሰለፉ አካላት ስለመኖራቸው ተናግረዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአደረጃጀት ልዩ እና በዘመናዊ ትጥቅ ተጠናክሮ በማንኛውም ሁኔታ ለሀገሩ ክብርና ሉአላዊነት መጠበቅ አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል። የ12ኛ ክፍል ፈተና በሳምንቱ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ስኬታማ በሆነ መልኩ ተከናውኗል። በሁሉም አካባቢዎች ተፈታኞች በበይነመረብ (ኦንላይን) እንዲሁም በወረቀት እንደየ ዝግጅቱና ምቹ ሁኔታውን መሰረት በማድረግ ፈተናውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በገጠር ኮሪደር አዲስ የህይወት ምእራፍ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የጊምቦ ወረዳ በተገነባው ሞዴል የገጠር መንደር የሚኖሩ አርሶ አደሮች አዲስ የህይወት ምእራፍ መጀመራቸውን ገልጸዋል። የኤሌክትሪክና ሌሎች አገልግሎቶች የተሟላለት የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር የአኗኗር ዘይቤያችንን ምቹና ዘመናዊ አድርጎታል ያሉት ነዋሪዎቹ ይህንን ላደረጉ ሁሉ እናመሰግናለን ብለዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ የተገነባውን የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የግብርናና ገጠር ሽግግርን እውን በማድረግ የአርሶ አደሩን አኗኗር ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ገልፀው የመብራት፣ የውሃ፣ የመንገድን ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን አርሶ አደሩ በአቅራቢያው ማግኘት የሚያስችልና የኢኮኖሚ አቅሙን የሚያሳድጉ መሆናቸውን በወቅቱ ተናግረዋል። በቀጣይም ተግባሩን በማስፋት ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግን ፍልሰት ለማስቀረት በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ አኔ ዲማ ወረዳ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰኣዳ አብዱረህማንና የከተማው ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎችም የአከባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰዓዳ አብዱረህማን በወቅቱ፤ ዛሬ የምንተክላቸው ችግኞች ለሀገራችን ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ የሚሰጡ ናቸው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለትውልድ ቀጣይነት አስተማማኝ ዋስትና ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)፤ በሸገር ከተማ የአካባቢውን አረንጓዴነት ለማረጋገጥና ኢኮኖሚውን ለመደገፍ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን የተለያዩ ዝርያ ያላቸውና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር ገብተናልም ብለዋል። የባቡር መስመር ጥገና የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በቅርቡ የጥገና ስራው የተጀመረውን የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ የባቡር መስመር ፕሮጀክት የጥገና ሂደት በዚሁ ሳምንት ጎብኝተዋል። ከአዋሽ -ኮምቦልቻ -ሃራ ገበያ 392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን ፕሮጀክት በአራት አቅጣጫ የጥገና ሥራው እየተከናወነ መሆኑም ታውቋል። ለልማት ተነሽዎች የተገነቡ ቤቶች በዚሁ ሳምንት የጅማ ከተማ አስተዳደር ለልማት ተነሺዎች ያስገነባውን 300 መኖሪያ ቤቶች መርቆ ማስረከቡን እንመለከታለን። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ፤ በክልሉ በገጠርም ይሁን በከተሞች ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሃ ቀመር፤ በከተማው በርካታ ፕሮጀክቶች በመንግስት እየተከናወኑ እንደሆኑና የተጠናቀቁትም ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በከተማዋ በዚህ አመት 80 የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ጠቅሰው ዛሬ ለልማት ተነሺዎች ተገንብተው የተላለፉ መኖሪያ ቤቶች የዚሁ ጥረት አንድ አካል ናቸው ብለዋል። እነዚህ መኖሪያ ቤቶች ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው ግንባታቸው ተጠናቆ ለ300 አባወራና እማወራዎች ተላልፈዋል ብለዋል።
ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች
Jun 29, 2026 3389
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • ምንድንነት የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም ‘አስም’ እንደሚባልም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የኪንታሮት ህመም እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? • ምልክቶች የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ጠቁመዋል። ምልክቶቹም በአብዛኛው በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ አስገንዝበዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር)፣ የእንስሳት አይነ ምድር ሽታዎች ለዚህኛው አስም አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን አስረድተዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑንም ተናግረዋል። • አጋላጭ (ለህመሙ መባባስ) መንስዔዎች አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የዓየር ብክለት፣ ጭስ)፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ዓይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? 👉ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎችዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ 👉 በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ 👉 በቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ ሙቀት የሚሰጡ መከላከያ ልብሶችን መልበስ፤ 👉 ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ • ሕክምናው የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የዓየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ከ 3 እስከ 10 በመቶ ያህሉ የዓለም ሕዝብ በአስም ተጠቂ መሆኑንም ጠቁመዋል። #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢዜአ #የጤና_ነገር
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 3115
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ከተጽዕኖ ፈጣሪነትና ተደማጭነት መጎልበት እስከ የአኅጉር ድምጽ መሆን - የኢትዮጵያን ታላቅነት የገለጠው የዲፕሎማሲው ዘርፍ ስኬት
Jun 25, 2026 3807
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቷ የፓን አፍካኒዝም ንቅናቄን በማንሳት አኅጉራዊ ተቋማት እንዲመሠረቱ ፊታውራሪ ከመሆን ጀምሮ ለጎረቤቶቿ ሰላም ጉልኅ ሚና ተጫውታለች፤ አሁንም ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔን እያሰረጸች በርካቶች እንዲጋሯት አድርጋለች። እንደ ሀገር ከለውጡ መንግሥት ወዲህ ከተገኙ በርካታ ትላልቅ ስኬቶች መካከል በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው አንዱ ነው። ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የለውጡ መንግሥት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ዋነኛ መለኪያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ነው። የኢትዮጵያ ሁኔታዎችን የማሰብ፣ የመፈለግና የመከወን ሂደት ንጥል (ለራስ ብቻ የሚል) ሳይሆን፤ በወንድማማችነት/እህትማማችነት ዕሳቤ በጋራ ማደግን ያነገበ ነው። ይህ ሂደቷም በበርካታ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ እንዲሁም አኅጉር አቀፍ ተቋማት ተወድሷል። በዚህም ሐሳቦቿ ቅቡል ሲሆኑ ተመልክተናል። ኢትዮጵያ የ#BRICS አባል መሆን መቻሏ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ይህም ተሰሚነቷን ያረጋገጠ ማስረጃ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ተያያዥ ጉዳዮች ዘርፈ-ብዙ ጥቅም በማስገኘት የበለጸገች ኢትየጵያን ዕውን የማድረግ ጉዞው ያፋጥናል። ወዲህ ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልና አፍሪካን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና መመረጧም የአኅጉሪቱ ድምጽ መሆኗን ይነግረናል። ዓለም አቀፍ ብሎም አኅጉር አቀፍ የሆኑ በርካታ ኮንፈረንሶችም በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እንዲካሄዱ መደረጉ አንድምታው ብዙ ነው። በብቃት ማስተናገዷ ደግሞ ሌላኛው ጥንካሬዋ። ሌላው የሀገራችንን የተጨበጠ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት የሚገልጽልን፤ የዓለም የዓየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን (COP32) እንድታዘጋጅ መመረጧ ነው። ይህን ትልቅ ዕድል በርካቶች ስለተመኙት አላገኙትም፤ ኢትዮጵያ ግን ዜጎቿን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባከናወነችው ያላሰለሰ ትጋት አግኝታዋለች። ግጭት ባለባቸው የቀጣናው ሀገራትም በመንግሥታቱ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት ሥር ከምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባለፈ፤ በግሏ የሰራችው ብዙ ነው። ከራሷ አልፋ ለጎረቤቶቿ ዘብ መሆኗ፤ በአብሮነት መኖርን እና በጋራ ማደግን በተግባር የገለጠች ሀገርም ያደርጋታል። ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ በሚለው ቅድሚያ ለሀገር በቀል ዕውቀቶች በሩን ክፍት ባደረገው ትጋቷም፤ በበርካታ የአኅጉሪቱ ሀገራት ዘንድ ምሥጋና አስችሯታል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲዋም በተለያዩ ሀገራት በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎቿን ከሀገራቱ እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመነጋገር በተሳካ ሁኔታ ልጆቿን ወደ ዕቅፏ መልሳለች፤ በቅርቡ በሳዑዲ ዓረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምኅረት ዐዋጅ እንዲሰጣቸው መደረጉ አንድ ማሳያ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን ጨምሮ በተለያዩ አኅጉራት በሚገኙ ሀገራት መሪዎችና ተወካዮች ዘንድ በስፋት የተመረጠችና የተጎበኘች ሀገር መሆኗን ማስታወስ ተገቢ ነው። ከጉብኝት ባለፈ ትላልቅ ስምምነቶችም የተፈራረመች መሆኗን ልብ ማለት ይገባል፤ ይህም የምታነሳውን ሐሳብ ገዥነትና የአፍሪካ መግቢያ በር መሆኗን ያሳያል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ መሆኑን መረዳት ይገባል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድርድር ሂደት የተጎናጸፈችው የዲፕሎማሲ ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መነቃቃት መፍጠሩንም ማጤን ያስፈልጋል። ይህ የተሳካው ሀገሪቱ ኢትዮጵያ መንገዷም የጋራ ልማትን የሰነቀ ዕውነት በመሆኑ ነው። በቀጣይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለአንዲት ሀገራቸው አምባሳደር በመሆን፤ የዲፕሎማሲውን ሥራ በይበልጥ ማገዝ ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ካልሠሩ ማን ለሀገራቸው ሊሠራ ይችላል?
ትንታኔዎች
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 1208
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 1626
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 1700
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 5413
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 7482
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 19087
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 12144
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 17898
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 3707
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 2869
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።