ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ነገሌ አርሲ መቀሌ 70 እንደርታን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ አደረገ 
Feb 5, 2026 24
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018 (ኢዜአ)፦‎ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገሌ አርሲ መቀሌ 70 እንደርታን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ርሆቦት ሰላሎ በ41ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። የመቀሌ 7ዐ እንደርታው ጋትሉዋክ ቱት በ62ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በሊጉ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ነገሌ አርሲ በ35 ነጥብ ደረጃውን ከአራተኛ ወደ ሶስተኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን አሳክቷል።   በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቀሌ 70 እንደርታ በ18 ነጥብ 17ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ተገኝቷል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ በተደረጉ የ18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ባህር ዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት አቻ ሲለያዩ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያ መድን እና ፋሲል ከነማ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአወያይ ስልጠና በሚቀጥሉት ሳምንታት ይጀመራል
Feb 5, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአጀንዳ ቀረፃ ማካሄድና የአወያይ ስልጠና በሚቀጥሉት ሳምንታት እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ገለጹ። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራሮች በሀገራዊ ምክክር ጉዳዮች ላይ በአዲስ አበባ በመወያየት ክልላዊና ሀገራዊ አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል።   በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ፤ በአራት ዓመታት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የተከናወኑ የሀገራዊ ምክክር ምዕራፎችን ገለፃ አድርገዋል። በሂደቱም የአማራ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ መካሄዱን ገልጸዋል። ከውይይቱ በተጓዳኝ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ማብራሪያ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት በጋራ ሆነው ያቀረቧቸው አጀንዳዎች የኮሚሽኑን አሳታፊነትና አካታችነት በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝነት እንዳላቸው ገልጸዋል።   በቀጣይም በትግራይ ክልል ለሚገኙ ወገኖች ተመሳሳይ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ምክክር ማካሄድ የሚያስችሉ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአጀንዳ ቀረፃ በማከናወንና በሚቀጥሉት ሳምንታት የአወያይ ስልጠናን በማስጀመር ለዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።   የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)፤ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት ለኮሚሽኑ ያቀረቧቸው አጀንዳዎች ከዚህ ቀደም ሲደረጉ የቆዩ ጥረቶች ውጤት ነው ብለዋል። በጫካ የነበሩ ታጣቂዎች ለኮሚሽኑ ያቀረቡት አጀንዳ ቀሪ በጫካ ለሚገኙ ታጣቂዎች ትምህርት እንደሚሆንም አስገንዝበዋል። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበርና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ፥ ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ አጀንዳዎችን በመሰነድ ለኮሚሽኑ አስረክብናል ብለዋል።   የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የእስካሁኑ ክንውኖች ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችሉ በመሆናቸው ቀሪ በጫካ የሚገኙ የሰላም አማራጭን እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በበኩላቸው፥ ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ ጉዳዮችን ከኢትዮጵያ ቀጣይ እጣ ፈንታ ጋር በማጤን የሰላም አማራጭን እንደተከተሉ ገልጸዋል።   በዚህም የተሳሳተ ትርክት፣ የሕገመንግስትና ተያያዥ ጉዳዮች የተካተቱባቸውን አጀንዳዎች በማደራጀት በጋራ የምክክር መድረክ መግባባትን መፍጠር የሚስችሉ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ እንዳስረከቡ ተናግረዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ እያሱ አባተ፥ በሰላም ስምምነቱ መነሻነት እንዲፈቱ የሚፈልጓቸውን የተቆጠሩ አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል።   በቀጣይም በሰላማዊ አማራጭ ለህዝብ ተጠቃሚነትና ለኢትዮጵያ ህልውና በሚበጁ ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በርክክብ ሥነስርዓቱ ማጠቃለያ ላይ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ፤ የድርጅቱ አመራር አባላት በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለመሳተፍ ለወሰዱት ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ማዕከሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ይደርስ የነበረውን መጉላላት አስቀርቷል
Feb 5, 2026 27
ባህር ዳር፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ ባህርዳር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ቀደም ሲል ይደርስ የነበረውን መጉላላት እንዳስቀረላቸው ተገልጋዮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትናንት በስቲያ በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ጊዜ ከመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራርያ፣ አገልግሎቱ የተጀመረበት ጊዜ አጭር ቢሆንም በዘርፉ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለና በቀጣይም የአገልግሎቱን ተደራሽነት ለማስፋት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።   ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር ቀደም ሲል ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት እንዳስቀረላቸው ገልጸዋል። ከማዕከሉ ተገልጋዮች መካከል አንዷለም ሞላ አንዱ ነው። እርሱ እንደሚለው፣ቀደም ሲል የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደ ክፍለ ከተማና ቀበሌ ሲሄድ ጉዳዩ ሳይፈጸም ተደጋጋሚ ቀጠሮ ብቻ ይሰጠው ነበር።   መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር የሚፈልገውን አገልግሎት በፍጥነት ማግኘት እንዳስቻለው ገልጿል።። ሌላው የማዕከሉ ተገልጋይ አታለል ሙሴ በአንድ ቦታ ላይ በቴክኖሎጂ የታገዘ በርካታ አገልግሎቶችን በማግኘቱ ጊዜውንና ወጪውን እንደቆጠበለት ተናግሯል።   አገልግሎቱ ቀደም ሲል ሲነሳ የነበረውን የመልካም አስተዳደርና የብልሹ አሰራር ችግሮችን በመፍታት ለተገልጋዩ እፎይታ የሰጠ መሆኑንም አመልክቷል። በማዕከሉ የሚፈልጉትን አገልግሎት በፍጥነት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላዋ ተጋልጋይ አለሚቱ ንጉሴ ናቸው።   እንዲህ አይነት አገልግሎቶች መጉላላትን በመቀነስ የህዝብን እርካታ የሚጨምሩ በመሆናቸው በሁሉም አካባቢዎች ሊሰፉ ይገባልም ብለዋል። የባህር ዳር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስተባባሪ ማስረሻ ፈንታ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ የ12 ተቋማት 65 አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ ታግዘው እየተሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። በማዕከሉ እየተሰጡ ከሚገኙ አገልግሎቶች መካከል የባንክ፣ የኢትዮ-ቴሌኮም፣ የትራንስፖርት፣ የመሬት ጉዳዮች፣ የንግድና የውሃና ፍሳሽ ይገኙበታል ብለዋል።   የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት መምሪያ ሃላፊ ጤናው ምህረቱ፤ ቀደም ሲል ሕብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ በርካታ ቅሬታዎች ሲያነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ በፍጥነትና በጥራት መስጠት መጀመሩ የተገልጋዮችን እንግልት በማስቀረት ቅሬታውን ፈቷል ብለዋል።   ማዕከሉ አሁን ለይ በቀን 325 ያህል ተገልጋዮችን እያስተናገደ መሆኑን ጠቅሰው፣ በቀጣይም አገልግሎቱን ለማስፋት ጥረት ይደረጋል ብለዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እተደረገ እንደሚገኝም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መግለጻቸው ይታወሳል።  
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሊያሸጋግር ነው
Feb 5, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሊያሸጋግር መሆኑን አስታወቀ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት ጋር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ለማሸጋገር የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።   ስምምነቱን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ጋር ተፈራርመዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ተቋማትን ወደ ዘመናዊ አሰራር ለማሸጋገር ጉዞ ጀምራለች። የፕላንና ልማት ሚኒስቴርም አሰራሩን ወደ ዲጂታል ለማሸጋገር ግብ ይዞ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬው ስምምነትም የዚሁ አካል ነው ብለዋል።   ስምምነቱ ሀገራዊ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ የልማት ስራዎች በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆናቸውን በዘመናዊ አሰራር ለመከታተል እና ለማረጋገጥ የዲጂታል ስርዓት መዘርጋት የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል። የልማት አስተዳደር ስራዎችና ፖሊሲዎች የሚያመጡትን ውጤት በትክክለኛ መረጃ ተመስርቶ ግምገማ ለማድረግ ትልቅ መሰረት የሚጥል መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡   የጥቅል አገራዊ ምርት ዕድገት እና ጥራትን ለመመዘንም ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል ብለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዮት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መረጃን ተንትኖ ስራ ላይ ማዋል ዘመናዊ መሰረተ ልማት የሚጠይቅ መሆኑን ጠቁመዋል።   በመሰል ስራ ላይ የተሰማራው ፕላንና ልማት ሚኒስቴር ስራው እንዲሳለጥ ፕሮጀክቱን ከተቀመጠው ጊዜ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ርብርብ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። ለዚህም የሁለቱም ተቋማት የቴክኒክ ኮሚቴ በጋራ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
የሚታይ
ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአወያይ ስልጠና በሚቀጥሉት ሳምንታት ይጀመራል
Feb 5, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአጀንዳ ቀረፃ ማካሄድና የአወያይ ስልጠና በሚቀጥሉት ሳምንታት እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ገለጹ። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራሮች በሀገራዊ ምክክር ጉዳዮች ላይ በአዲስ አበባ በመወያየት ክልላዊና ሀገራዊ አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል።   በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ፤ በአራት ዓመታት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የተከናወኑ የሀገራዊ ምክክር ምዕራፎችን ገለፃ አድርገዋል። በሂደቱም የአማራ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ መካሄዱን ገልጸዋል። ከውይይቱ በተጓዳኝ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ማብራሪያ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት በጋራ ሆነው ያቀረቧቸው አጀንዳዎች የኮሚሽኑን አሳታፊነትና አካታችነት በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝነት እንዳላቸው ገልጸዋል።   በቀጣይም በትግራይ ክልል ለሚገኙ ወገኖች ተመሳሳይ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ምክክር ማካሄድ የሚያስችሉ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአጀንዳ ቀረፃ በማከናወንና በሚቀጥሉት ሳምንታት የአወያይ ስልጠናን በማስጀመር ለዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።   የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)፤ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት ለኮሚሽኑ ያቀረቧቸው አጀንዳዎች ከዚህ ቀደም ሲደረጉ የቆዩ ጥረቶች ውጤት ነው ብለዋል። በጫካ የነበሩ ታጣቂዎች ለኮሚሽኑ ያቀረቡት አጀንዳ ቀሪ በጫካ ለሚገኙ ታጣቂዎች ትምህርት እንደሚሆንም አስገንዝበዋል። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበርና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ፥ ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ አጀንዳዎችን በመሰነድ ለኮሚሽኑ አስረክብናል ብለዋል።   የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የእስካሁኑ ክንውኖች ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችሉ በመሆናቸው ቀሪ በጫካ የሚገኙ የሰላም አማራጭን እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በበኩላቸው፥ ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ ጉዳዮችን ከኢትዮጵያ ቀጣይ እጣ ፈንታ ጋር በማጤን የሰላም አማራጭን እንደተከተሉ ገልጸዋል።   በዚህም የተሳሳተ ትርክት፣ የሕገመንግስትና ተያያዥ ጉዳዮች የተካተቱባቸውን አጀንዳዎች በማደራጀት በጋራ የምክክር መድረክ መግባባትን መፍጠር የሚስችሉ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ እንዳስረከቡ ተናግረዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ እያሱ አባተ፥ በሰላም ስምምነቱ መነሻነት እንዲፈቱ የሚፈልጓቸውን የተቆጠሩ አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል።   በቀጣይም በሰላማዊ አማራጭ ለህዝብ ተጠቃሚነትና ለኢትዮጵያ ህልውና በሚበጁ ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በርክክብ ሥነስርዓቱ ማጠቃለያ ላይ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ፤ የድርጅቱ አመራር አባላት በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለመሳተፍ ለወሰዱት ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሊያሸጋግር ነው
Feb 5, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሊያሸጋግር መሆኑን አስታወቀ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት ጋር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ለማሸጋገር የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።   ስምምነቱን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ጋር ተፈራርመዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ተቋማትን ወደ ዘመናዊ አሰራር ለማሸጋገር ጉዞ ጀምራለች። የፕላንና ልማት ሚኒስቴርም አሰራሩን ወደ ዲጂታል ለማሸጋገር ግብ ይዞ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬው ስምምነትም የዚሁ አካል ነው ብለዋል።   ስምምነቱ ሀገራዊ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ የልማት ስራዎች በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆናቸውን በዘመናዊ አሰራር ለመከታተል እና ለማረጋገጥ የዲጂታል ስርዓት መዘርጋት የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል። የልማት አስተዳደር ስራዎችና ፖሊሲዎች የሚያመጡትን ውጤት በትክክለኛ መረጃ ተመስርቶ ግምገማ ለማድረግ ትልቅ መሰረት የሚጥል መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡   የጥቅል አገራዊ ምርት ዕድገት እና ጥራትን ለመመዘንም ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል ብለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዮት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መረጃን ተንትኖ ስራ ላይ ማዋል ዘመናዊ መሰረተ ልማት የሚጠይቅ መሆኑን ጠቁመዋል።   በመሰል ስራ ላይ የተሰማራው ፕላንና ልማት ሚኒስቴር ስራው እንዲሳለጥ ፕሮጀክቱን ከተቀመጠው ጊዜ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ርብርብ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። ለዚህም የሁለቱም ተቋማት የቴክኒክ ኮሚቴ በጋራ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
መንግስት የህዝብን የልማት ጥያቄ እየመለሰ ነው -  አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Feb 5, 2026 69
ሻኪሶ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት የህዝብን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ እንደሚገኝ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ፡፡ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ድጋፍ የሚገነባው የሻኪሶ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተገኙበት የግንባታ ስራ ተጀምሯል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት መንግስት የህዝብን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡   ዛሬ የግንባታ ስራው የተጀመረው የሻኪሶ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክትም አካባቢው በቡና፣ በማዕድናትና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የአውሮፕላን ማረፊያው መገንባት የአካባቢውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያሳልጥ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አካባቢውን ለማልማት ላደረገው ዕገዛ ያመሰገኑት አቶ ሽመልስ፤ የአውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክቱን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ርብርብ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፤ አየር መንገዱ አዲስ አበባን ከሀገር ውስጥ ከተሞች ጋር የሚያገናኙ በርካታ በረራዎች እንዳሉት ጠቁመዋል።   የሻኪሶ አውሮፕላን ማረፊያም ተጨማሪ የአየር መንገዱ መዳረሻ በማድረግ የጉጂ ዞን የተፈጥሮ ሀብትን ለማልማት ተደማሪ አቅም እንደሚሆን አስረድተዋል። ፕሮጀክቱ ተጠናቆ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ሲጀመር የአካባቢውን ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማቀላጠፍና የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ የራሱ ድርሻ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው፤ ከዚህ በፊት በስፍራው የአውሮፕላን መንደርደሪያ እንደነበር አስታውሰው የክልሉ መንግስት የአውሮፕላን መንደርደሪያውን ወደ ንግድ አውሮፕላን ማረፊያነት ለመቀየር ያቀረበውን ጥሪ በመቀበል ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ግንባታውን ማስጀመሩን ገልፀዋል፡፡   ፕሮጀክቱ ተጠናቆ በተያዘለት ጊዜ አገልግሎት እንዲጀምርም የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡ የሻኪሶ አውሮፕላን ማረፊያ በ124 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሚገነባ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ በይፋዊ የግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የፌዴራል፣ የክልልና የጉጂ ዞን አመራሮች እንዲሁም አባገዳዎች ተገኝተዋል፡፡
በቡና ዘርፍ የተከናወኑ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለውጭ ምንዛሬ ገቢ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል
Feb 5, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ በቡና ዘርፍ የተከናወኑ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለውጭ ምንዛሬ ገቢ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ከምስራቅ አፍሪካ ፋይን ኮፊ ማህበር (AFCA) ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 22ኛው የአፍሪካ ፋይን ኮፊ (Africa Fine Coffee) ኤግዚቢሽንና ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።   ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በጀመረው በዚህ መድረክ ላይ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፣ የዘርፉ ተመራማሪዎችና ዓለም አቀፍ እንግዶች ተገኝተዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት 469ሺህ ቶን ቡና ለዓለም ገበያ በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን ገልጸዋል፡፡ ይህ ውጤት በሀገሪቱ የቡና ታሪክ ከፍተኛው የገቢና የጥራት መጠን ሆኖ መመዝገቡን ጠቅሰው፤ በያዝነው ዓመት የሚገኘውን ገቢ ወደ 3 ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለቡና ዘርፉ ዕድገት ትልቅ ድርሻ ማበርከቱንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ካለው የዓረቢካ ቡና ዝርያ 90 በመቶ የሚሆነውን የጄኔቲክ ብዝሃ-ህይወት በመያዟ ለዓለም የቡና ኢንዱስትሪ እንደ ዘር ባንክ እንደምትቆጠርም ተናግረዋል፡፡ ይህም ለተለዋዋጭ የአየር ንብረት የማይበገሩ ዝርያዎችን ለማምረት ልዩ ዕድል መፍጠሩን ተናግረው፤ ጥሬ ቡናን ከመላክ ባለፈ እሴት የተጨመረበት ቡናን ወደ ውጭ ለመላክ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና አማካኝነት በአህጉሪቱ ውስጥ የቡና ንግድን ለማጠናከር የፖሊሲ ማሻሻያዎች እየተደረጉ መሆናቸውንም እንዲሁ፡፡ የቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሻፊ ዑመር፤ መንግስት በቡናው ዘርፍ የጀመረው የሪፎርም ስራ አስደናቂ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል።   ይህ የለውጥ እርምጃ ከአምራች አርሶ አደሩ ጀምሮ በንግድ ሰንሰለቱ ውስጥ ያሉ አካላትን ተጠቃሚነት በእጅጉ ማሳደጉን ገልጸዋል። እየተካሄደ የሚገኘው ጉባኤ አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ተጠቅማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የቡና ገበያ ድርሻ እንድታሳድግ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር አስገንዝበዋል። የአፍካ (AFCA) ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ጊልበርት ጋታሊ በዚሁ ጊዜ በአፍሪካ የቡና ዘርፍን ለማዘመንና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን ለማረጋገጥ ከአጋር ድርጅቶች ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።‎   በተጨማሪም ለላኪዎች፣ ለገዢዎች፣ ለማሽን አምራቾች፣ ለቡና ጥራት ባለሙያዎች እና በጥቅሉ በዘርፉ ኢንዱስትሪው የአቅርቦትና የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ላሉ አካላት ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ኤግዚቢሽንና ኮንፍረንሱ ከዘርፉ ተዋናዮች ጋር ጠንካራ ትስስር በመፍጠር የአፍሪካን የቡና ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ትልቅ አቅም እንደሚሆን አመልክተዋል።
ኢንስቲትዩቱን የልህቀት ማእከል ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት ይጠናከራሉ   
Feb 5, 2026 60
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩትን አቅምና አደረጃጀት በማጎልበት የልህቀት ማእከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ገለጹ። የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት የሪፎርም፣ የአዲስ ሎጎ ማስተዋወቂያና በፍትህ ዘርፉ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለሙያዎችና አመራሮች እውቅና የመስጠት መርሃግብር የፍትህ ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል። በመርሃግብሩ ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ በአዲስ አደረጃጀት ወደ ስራ ገብቷል።   ኢንስቲትዩቱ ተጠሪነቱ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መደረጉ የምርምርና የስልጠና ስራዎች ከፍትህ አካላት ጋር በተጣጣመና በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል ያስችላል ብለዋል። አደረጃጀቱ የተቋሙን አገልግሎት ለማሻሻልና ለማቀላጠፍ እንዲሁም የህግ አወጣጥና አፈጻጸም ችግሮችን ለመፍታት የተቋሙን አቅም የሚያጠናክር ነው ብለዋል። የኢንስቲትዩቱን የአቅም ግንባታ፣ የምርምርና የመረጃ ማእከል ስራዎችን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት አዲስ ሎጎ ይፋ የተደረገ ሲሆን ይህም የኢንስቲትዩቱን የልህቀት ማዕከልነት ለማጎልበት ከሚከናወኑ ስራዎች ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል።   የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አበባ እምቢያለ በበኩላቸው፤ የኢንስቲትዩቱና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትብብር ማእቀፍ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።   ይህም በፍትህ ሰርዓቱ የሚከናወኑ የለውጥ ስራዎች ጠንካራ የምርምርና የፖሊሲ መሰረት እንዲኖራቸውና ኢንስቲትዩቱን የልህቀት ማእከል ለማድረግ የሚከናወኑ ስራዎች ላይ ጉልህ ሚና ያለው በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ መዋቅራዊ ተግዳሮቶችን በመፍታት ወደ ሁሉ አቀፍ የለውጥ ምእራፍ ተሸጋግሯል ።   የሶስት አመታት ፍኖተ ካርታና ስትራቴጂክ እቅድ ተዘጋጅቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በኢንስቲትዩቱ ከ80 በላይ ጥናቶችና ምርምሮች መካሄዳቸውን ገልጸው፤ በፍትሐብሔር ፣ በወንጀል ፣ባህላዊ ፍትህ አስተዳደር ፣ ሰብአዊ መብትና ሌሎች ጉዳዮች ለይ ምርምር ከተከናወነባቸው ጉዳዮች መካከል ለአብነት ጠቅሰዋል። ባለፉት ዓመታት ከ25 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የፍትህ ዘርፍ ባለሙያዎችና አመራሮች ስልጠና መሰጠቱንም አክለዋል። ኢንስቲትዩቱ ዘመኑ የሚጠይቀውን የእውቀት፣ የክህሎትና የቴክኖሎጂ የልህቀት ማእከል ለመሆን እየሰራ ነው ብለዋል። የስልጠና ማእከሉን ምቹ የማድረግ ፣ የኢ-ለርኒንግ ስቱዲዮ የማዘጋጀት ፣ የመረጃ ማእከል የማደራጀት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአወያይ ስልጠና በሚቀጥሉት ሳምንታት ይጀመራል
Feb 5, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአጀንዳ ቀረፃ ማካሄድና የአወያይ ስልጠና በሚቀጥሉት ሳምንታት እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ገለጹ። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራሮች በሀገራዊ ምክክር ጉዳዮች ላይ በአዲስ አበባ በመወያየት ክልላዊና ሀገራዊ አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል።   በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ፤ በአራት ዓመታት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የተከናወኑ የሀገራዊ ምክክር ምዕራፎችን ገለፃ አድርገዋል። በሂደቱም የአማራ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ መካሄዱን ገልጸዋል። ከውይይቱ በተጓዳኝ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ማብራሪያ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት በጋራ ሆነው ያቀረቧቸው አጀንዳዎች የኮሚሽኑን አሳታፊነትና አካታችነት በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝነት እንዳላቸው ገልጸዋል።   በቀጣይም በትግራይ ክልል ለሚገኙ ወገኖች ተመሳሳይ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ምክክር ማካሄድ የሚያስችሉ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአጀንዳ ቀረፃ በማከናወንና በሚቀጥሉት ሳምንታት የአወያይ ስልጠናን በማስጀመር ለዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።   የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)፤ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት ለኮሚሽኑ ያቀረቧቸው አጀንዳዎች ከዚህ ቀደም ሲደረጉ የቆዩ ጥረቶች ውጤት ነው ብለዋል። በጫካ የነበሩ ታጣቂዎች ለኮሚሽኑ ያቀረቡት አጀንዳ ቀሪ በጫካ ለሚገኙ ታጣቂዎች ትምህርት እንደሚሆንም አስገንዝበዋል። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበርና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ፥ ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ አጀንዳዎችን በመሰነድ ለኮሚሽኑ አስረክብናል ብለዋል።   የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የእስካሁኑ ክንውኖች ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችሉ በመሆናቸው ቀሪ በጫካ የሚገኙ የሰላም አማራጭን እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በበኩላቸው፥ ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ ጉዳዮችን ከኢትዮጵያ ቀጣይ እጣ ፈንታ ጋር በማጤን የሰላም አማራጭን እንደተከተሉ ገልጸዋል።   በዚህም የተሳሳተ ትርክት፣ የሕገመንግስትና ተያያዥ ጉዳዮች የተካተቱባቸውን አጀንዳዎች በማደራጀት በጋራ የምክክር መድረክ መግባባትን መፍጠር የሚስችሉ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ እንዳስረከቡ ተናግረዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ እያሱ አባተ፥ በሰላም ስምምነቱ መነሻነት እንዲፈቱ የሚፈልጓቸውን የተቆጠሩ አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል።   በቀጣይም በሰላማዊ አማራጭ ለህዝብ ተጠቃሚነትና ለኢትዮጵያ ህልውና በሚበጁ ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በርክክብ ሥነስርዓቱ ማጠቃለያ ላይ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ፤ የድርጅቱ አመራር አባላት በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለመሳተፍ ለወሰዱት ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ወጥነት ያለው የአሰራርን በማስፈን ዘመናዊ የክትትል ስርዓት ለመዘርጋት ያግዛል 
Feb 5, 2026 59
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓትን በማስፈን ዘመናዊ የክትትል ስርዓት ለመዘርጋት ያግዛል ሲሉ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል ገለጹ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአይነቱ ለየት ያለ አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል።   የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል ፣ ተቋሙ የሪፎርም ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል። በሪፎርሙ በተለይም የተቋሙን አሰራር በቴክኖሎጂ ማዘመን በመቻሉ በወንጀል መከላከል ረገድ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን አስታውቀዋል። በዛሬው እለት ይፋ የተደረገው አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳም ከቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ የተቋሙን የመፈጸም አቅም በእጅጉ የሚያልቅ መሆኑን አንስተዋል።   ቀደም ሲል የነበረው የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ወጥ የሆነ ቁጥጥር ለማድረግ ምቹ እንዳልነበር አውስተዋል። አዲሱ ታርጋ የፌደራል ፖሊስን መለያ ምልክት፣ ሚስጥራዊ ኮድንና ዲጂታላይዜሽንን ያካተተ መሆኑ ከቀድሞው ለየት ያለ እና ዓለም አቀፍ ስታንዳርድን የጠበቀ ነው ብለዋል። በዚህም ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት በማስፈን ዘመናዊ የክትትል ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያግዝ አመላክተዋል። የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴዔታ በረኦ ሀሰን በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች ተመዝግበው ይገኛሉ ብለዋል።   የእነዚህን ተሽከርካሪዎች ስምሪት በአግባቡ ለማስተዳደር ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና አሰራሩን ማዘመን ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በቅርቡም አዲሱን ሀገር አቀፍ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ይፋ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዛሬው እለት ይፋ ያደረገው አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ የተቋሙን የሪፎርም ጉዞ ስኬት የሚያሳይ መሆኑንም ገልፀዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና ዳኞችን ሹመት አፀደቀ
Feb 5, 2026 80
አዲስ አበባ፤ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና 50 የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት አፀደቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ በ11ኛ መደበኛ ስብሰባው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት አፅድቋል።   በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ምህረቱ ሻንቆ (ዶ/ር) የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን የስራ ልምድ ባቀረቡበት ወቅት ተሿሚዎች በትምህርት ዝግጅታቸው እና በስራ ልምዳቸው ለፍትህ ስርዓቱ ሁለንተናዊ ለውጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ እየተካሄደ ባለው የፍትህ ስርዓት ማሻሻያ አስተማማኝ የዳኝነት ስርዓትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡   በዚህም በፍርድ ቤቶች ዘመናዊ፣ ግልጽ፣ ነጻና ገለልተኛ አሰራር በመዘርጋት ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች እያከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና 50 የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመትን አፅድቋል፡፡ በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ በቀረቡለት ዕጩዎች ላይ ተወያይቶ የአቶ ልዑል ካህሳይን እና የአቶ ምትኩ ማዳን ሹመት ውሳኔ ቁጥር 6/ 2018 አድርጎ አጽድቋል። በተመሳሳይም ምክር ቤቱ በቀረቡለት 50 የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዕጩ ዳኞች ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ የቀረቡለትን ዕጩዎች ሹመት የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 7/2018 በማድረግ አጽድቋል።
ለዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ምርጫ እውን መሆን የመገናኛ ብዙሃን ኃላፊነት ድርብ ነው
Feb 5, 2026 78
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ ለዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ምርጫ እውን መሆን የመገናኛ ብዙሃን ኃላፊነት ድርብ መሆኑን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24/2018 ዓም ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅቶች እያደረገ ሲሆን የዕጩዎች ምዝገባም እየተከናወነ ይገኛል። በመጪው ጠቅላላ ምርጫ የመገናኛ ብዙሃን ድርሻን አስመልክቶ ኢዜአ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ትምህርት ክፍል መምህራንን አነጋግሯል። በዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ ተሻለ ተገኔ(ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በንቃት እንዲሳተፉ መገናኛ ብዙሃን ትክክለኛ መረጃ በመስጠት የምርጫ ህጉን በተመለከተ ግንዛቤ ማሳደግ ላይ ትኩረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።   በምርጫ ወቅት መራጮች በበቂ መረጃ ላይ ተመስርተው ድምጽ እንዲሰጡ የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም አክለዋል። የምርጫው ሂደት ትክክለኛ፣ ዴሞክራሲያዊና አካታች መሆኑን በመከታተልና የተቀመጡ የስነ ምግባር መርሆዎችን ተከትሎ መረጃ በመስጠት ህዝቡ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ ይገባቸዋል ነው ያሉት። የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ሂደቱን በመከታተል ለመራጩ ህዝብ ግንዛቤ በመፍጠር ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ በሚበጅ መልኩ አበክረው መስራት እንዳለባቸውም ጠቅሰዋል።   ምርጫው ተዓማኒ እንዲሆን የመገናኛ ብዙሃን ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የህዝብ ግንኙነትና ስነ ተግባቦት ትምህርት ክፍል ኃላፊና መምህር ወገኔ ዳንኤል ናቸው። መገናኛ ብዙሃን እና የሚዲያ ባለሙያዎች በምርጫ ዘገባ ወቅት ሙያዊ የስነ ምግባር መርሆዎችን ተከትለው የመስራት ግዴታ እንዳለባቸውም ነው ያመለከቱት።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየሰራን ነው - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Feb 5, 2026 60
ሐረር፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየሰሠሩ መሆኑን በሐረሪ ክልል በምርጫው የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከትናንት በስቲያ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የመንግስትን የ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ጊዜ መንግስት ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ፣ አካታች እንዲሁም ከባለፈው ምርጫ በሁሉም መስፈርት የተሻለ እንዲሆን አበክሮ እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። በሐረሪ ክልል የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እያደረጉት ያለውን ዝግጅት አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮዽያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ(ኢብአፓ) የሐረሪ ክልልና ድሬዳዋ አስተዳደር አስተባባሪ ሐሰነት ሙሜ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖለቲካ ምሕዳሩን ለማስፋትና የመድበለ-ፓርቲ ሥርዓትን ለማጠናከር የጋራ ምክር ቤት መመስረታቸውን አስታውሰዋል። የምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎች ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑንጠቁመው በዚህም ምክር ቤቱ 6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሚናውን ተጫውቷል ብለዋል። አክለውም ምክር ቤቱ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሕዝብ ዘንድ ተዓማኒነት ያለው እንዲሆን ለፓርቲ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከመስጠት ጀምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አመልክተዋል። ምክር ቤቱ አሁን ላይ 12 የፖለቲካ ፓርቲዎችን በአባልነት የያዘ ሲሆን በቀጣይ ሌሎች ፓርቲዎችንም የምክር ቤቱ አባል ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዳይሬክተር ሐሰን አብዲ 6ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከተደረጉ ምርጫዎች በተሻለ መልኩ አሳታፊ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህም ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የድርሻውን መወጣቱን አስታውሰዋል። አቶ ሐሰን አክለውም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም መመዘኛዎች ካለፉት ምርጫዎች በተሻለ አሳታፊ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢና የክልሉ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ(ነእፓ) ምክትል ሰብሳቢ አብዱልሃፊዝ አህመድ ፓርቲያቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።   ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለሀገሪቱ የዴሞክራሲ ግንባታ የድርሻቸውን ከሚወጡባቸው ጉዳዮች አንዱ ምርጫ እንደመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ሁሉን አሳታፊና ፍትሃዊ እንዲሆን የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ጥረት እያደረገ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
በመግባባት ላይ የተመሰረተ የምክክር ሂደት ማካሄድ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ መስጠት ነው
Feb 5, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ ብሔራዊ መግባባትን ለማጠናከር በመግባባት ላይ የተመሰረተ የምክክር ሂደት ማካሄድ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ መስጠት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።   በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ኮሚሽኑ በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የተከናወኑ ተግባራትን ገለፃ አድርገዋል። ኢትዮጵያ ያለፈችባቸው የግጭት አዙሪት የተሳሳቱ መንገዶች በሀገራዊ ምክክር መፍትሔ ሊያገኙ እንደሚገባ የዘመናት ጥያቄ ሆኖ መቆየቱን ተናግረዋል። ዘላቂ ብሔራዊ መግባባትን ለማምጣት ምክክር አስፈላጊ ነው ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፥ ምክክርም በመግባባት ላይ የተመሰረተ ሂደትን የሚፈልግ ጉዳይ ነው ብለዋል። በዚህም የአማራ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ መካሄዱን ገልጸዋል። የነፍጥ ትግል አሸናፊና ተሸናፊን የሚፈጥር እንጂ ሀገራዊ መግባባትን የሚያሰፍን እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ታጣቂ ኃይል የትጥቅ ትግልን አስከፊነት በቅጡ በመገንዘብ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ ይሰጣል ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፥ አጀንዳዎችን በመለየት በምክክር መፍትሔ ያገኛሉ በሚል ለወሰዱት ቁርጠኛ አቋም ምስጋና አቅርበዋል። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበርና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ፥ የትጥቅ ትግል ህዝብን ከማጎሳቆል ያለፈ ፋይዳ እንደሌለው በመገንዘብ የሰላም ስምምነት መውሰዳቸውን አስታውሰዋል። በዚህም ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ ጉዳዮችን በመሰነድ ለአማራ ህዝብና ኢትዮጵያ ችግር የሆኑ አጀንዳዎች በምክክር መፍትሔ እንደሚያገኙ በማመን ለይተው ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል። በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የእስካሁኑ ክንውኖች የተደረገላቸው ገለፃም በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል ሂደቶችን እንዳለፈ መገንዘባቸውን ተናግረዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፥ የሶስት ዓመታት የትጥቅ ትግላቸውን በሚገባ በማጤን አሉኝ የሚሏቸውን ጉዳዮች በሰላማዊ መንገድ መፍትሔ ለማስገኘት የሰላም አማራጭን እንደተከተሉ ገልጸዋል።   የተሳሳተ ትርክት፣ የሕገመንግስት እና ተያያዥ ጉዳዮች የተካተቱባቸውን አጀንዳዎች በማደራጀት በጋራ የምክክር መድረክ መግባባትን በመፍጠር በሂደት መፍትሔ እንደሚያገኙ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር እያሱ አባተ፥ ከመንግስት ጋር ከደረሱት የሰላም ስምምነት በተጨማሪ አሉኝ የሚሏቸውንና እንዲፈቱ የሚፈልጓቸውን የተቆጠሩ አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል። ዓመታትን በተሻገረው የግጭት ቆይታቸው ህዝብን ከማጎሳቆል የዘለለ ፋይዳ እንዳልሰጠ ገልጸዋል። በቀጣይም በሰላማዊ አማራጭ ለህዝብ ተጠቃሚነትና ኢትዮጵያ ህልውና በሚበጁ ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ሌሎች በጫካ የሚገኙ ቀሪ ታጣቂዎችም የሰላም አማራጭን በመከተል ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ የመከላከያ የጋራ ኮሚቴ ስብሰባ በስኬት ተጠናቀቀ
Feb 5, 2026 56
የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ የመከላከያ የጋራ ኮሚቴ ስብሰባ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያና ኬንያ የመከላከያ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው 1ኛ መደበኛ የኢትዮ-ኬንያ የመከላከያ የጋራ ኮሚቴ ስብሰባ በስኬት ተጠናቋል። በመተማመን፣ በመከባበርና በጋራ ጥቅም መርህ ላይ የተመሰረተው የኢትዮጵያ እና የኬንያ መከላከያ የሁለትዮሽ ግንኙነት የሁለቱን ሀገራት ጥቅም የሚያስጠብቅ መሆኑን የኢትዮጵያን መከላከያ ልዑክ የመሩት የመከላከያ የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬከተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ ገልፀዋል።   ሜጄር ጄኔራል ተሾመ በውይይቱ ወቅት የቀረቡ አጀንዳዎች የሁለቱን ሀገራት የአጋርነትና የአብሮነት ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ከመሆናቸውም በላይ የቀጣናው አሁናዊ ሁኔታ የሚጠይቀውን የጋራ ተሳትፎ አስመልክቶ ጠንካራ አቋም እንዲያዝ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን አንስተዋል ብለዋል። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በጠንካራ የሁለትዮሽ ትብብራችንና ውጤታማነታችን በማያስደስታቸው አካላት እኩይ ተግባር ሳንዘናጋ የየበኩላችንን መወጣት አለብን ሲሉም ተናግረዋል።   ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ መከላከያ የበኩሉን ድርሻ በተመለከተ በኃላፊነት ስሜት፣ በትጋትና በውጤታማነት መወጣት የሚያስችል የላቀ ዝግጁነት እንዳለውም አረጋግጠዋል። የኬንያ የመከላከያ ኦፕሬሽን፣ ኢንዶክትሪኔሽን እና ስልጠና ኃላፊ ሜጀር ጄኔራል ሉዋሬ በበኩላቸው፤ ሁለቱ ሀገራት ለዘመናት የቆየ ጠንካራ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ያላቸው ከመሆናቸው በላይ በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በኢነርጂ ዘርፍ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው አስረድተዋል።     ይህ መድረክ የሁለቱን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ የሰላም እና ጸጥታ ዘርፎች የሚደረገውን ግንኙነት እና ትብብር በማጠናከር በኩል ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፖለቲካ
ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአወያይ ስልጠና በሚቀጥሉት ሳምንታት ይጀመራል
Feb 5, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአጀንዳ ቀረፃ ማካሄድና የአወያይ ስልጠና በሚቀጥሉት ሳምንታት እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ገለጹ። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራሮች በሀገራዊ ምክክር ጉዳዮች ላይ በአዲስ አበባ በመወያየት ክልላዊና ሀገራዊ አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል።   በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ፤ በአራት ዓመታት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የተከናወኑ የሀገራዊ ምክክር ምዕራፎችን ገለፃ አድርገዋል። በሂደቱም የአማራ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ መካሄዱን ገልጸዋል። ከውይይቱ በተጓዳኝ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ማብራሪያ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት በጋራ ሆነው ያቀረቧቸው አጀንዳዎች የኮሚሽኑን አሳታፊነትና አካታችነት በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝነት እንዳላቸው ገልጸዋል።   በቀጣይም በትግራይ ክልል ለሚገኙ ወገኖች ተመሳሳይ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ምክክር ማካሄድ የሚያስችሉ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአጀንዳ ቀረፃ በማከናወንና በሚቀጥሉት ሳምንታት የአወያይ ስልጠናን በማስጀመር ለዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።   የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)፤ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት ለኮሚሽኑ ያቀረቧቸው አጀንዳዎች ከዚህ ቀደም ሲደረጉ የቆዩ ጥረቶች ውጤት ነው ብለዋል። በጫካ የነበሩ ታጣቂዎች ለኮሚሽኑ ያቀረቡት አጀንዳ ቀሪ በጫካ ለሚገኙ ታጣቂዎች ትምህርት እንደሚሆንም አስገንዝበዋል። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበርና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ፥ ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ አጀንዳዎችን በመሰነድ ለኮሚሽኑ አስረክብናል ብለዋል።   የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የእስካሁኑ ክንውኖች ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችሉ በመሆናቸው ቀሪ በጫካ የሚገኙ የሰላም አማራጭን እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በበኩላቸው፥ ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ ጉዳዮችን ከኢትዮጵያ ቀጣይ እጣ ፈንታ ጋር በማጤን የሰላም አማራጭን እንደተከተሉ ገልጸዋል።   በዚህም የተሳሳተ ትርክት፣ የሕገመንግስትና ተያያዥ ጉዳዮች የተካተቱባቸውን አጀንዳዎች በማደራጀት በጋራ የምክክር መድረክ መግባባትን መፍጠር የሚስችሉ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ እንዳስረከቡ ተናግረዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ እያሱ አባተ፥ በሰላም ስምምነቱ መነሻነት እንዲፈቱ የሚፈልጓቸውን የተቆጠሩ አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል።   በቀጣይም በሰላማዊ አማራጭ ለህዝብ ተጠቃሚነትና ለኢትዮጵያ ህልውና በሚበጁ ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በርክክብ ሥነስርዓቱ ማጠቃለያ ላይ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ፤ የድርጅቱ አመራር አባላት በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለመሳተፍ ለወሰዱት ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ወጥነት ያለው የአሰራርን በማስፈን ዘመናዊ የክትትል ስርዓት ለመዘርጋት ያግዛል 
Feb 5, 2026 59
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓትን በማስፈን ዘመናዊ የክትትል ስርዓት ለመዘርጋት ያግዛል ሲሉ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል ገለጹ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአይነቱ ለየት ያለ አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል።   የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል ፣ ተቋሙ የሪፎርም ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል። በሪፎርሙ በተለይም የተቋሙን አሰራር በቴክኖሎጂ ማዘመን በመቻሉ በወንጀል መከላከል ረገድ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን አስታውቀዋል። በዛሬው እለት ይፋ የተደረገው አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳም ከቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ የተቋሙን የመፈጸም አቅም በእጅጉ የሚያልቅ መሆኑን አንስተዋል።   ቀደም ሲል የነበረው የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ወጥ የሆነ ቁጥጥር ለማድረግ ምቹ እንዳልነበር አውስተዋል። አዲሱ ታርጋ የፌደራል ፖሊስን መለያ ምልክት፣ ሚስጥራዊ ኮድንና ዲጂታላይዜሽንን ያካተተ መሆኑ ከቀድሞው ለየት ያለ እና ዓለም አቀፍ ስታንዳርድን የጠበቀ ነው ብለዋል። በዚህም ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት በማስፈን ዘመናዊ የክትትል ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያግዝ አመላክተዋል። የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴዔታ በረኦ ሀሰን በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች ተመዝግበው ይገኛሉ ብለዋል።   የእነዚህን ተሽከርካሪዎች ስምሪት በአግባቡ ለማስተዳደር ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና አሰራሩን ማዘመን ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በቅርቡም አዲሱን ሀገር አቀፍ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ይፋ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዛሬው እለት ይፋ ያደረገው አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ የተቋሙን የሪፎርም ጉዞ ስኬት የሚያሳይ መሆኑንም ገልፀዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና ዳኞችን ሹመት አፀደቀ
Feb 5, 2026 80
አዲስ አበባ፤ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና 50 የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት አፀደቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ በ11ኛ መደበኛ ስብሰባው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት አፅድቋል።   በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ምህረቱ ሻንቆ (ዶ/ር) የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን የስራ ልምድ ባቀረቡበት ወቅት ተሿሚዎች በትምህርት ዝግጅታቸው እና በስራ ልምዳቸው ለፍትህ ስርዓቱ ሁለንተናዊ ለውጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ እየተካሄደ ባለው የፍትህ ስርዓት ማሻሻያ አስተማማኝ የዳኝነት ስርዓትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡   በዚህም በፍርድ ቤቶች ዘመናዊ፣ ግልጽ፣ ነጻና ገለልተኛ አሰራር በመዘርጋት ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች እያከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን እና 50 የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመትን አፅድቋል፡፡ በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ በቀረቡለት ዕጩዎች ላይ ተወያይቶ የአቶ ልዑል ካህሳይን እና የአቶ ምትኩ ማዳን ሹመት ውሳኔ ቁጥር 6/ 2018 አድርጎ አጽድቋል። በተመሳሳይም ምክር ቤቱ በቀረቡለት 50 የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዕጩ ዳኞች ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ የቀረቡለትን ዕጩዎች ሹመት የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 7/2018 በማድረግ አጽድቋል።
ለዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ምርጫ እውን መሆን የመገናኛ ብዙሃን ኃላፊነት ድርብ ነው
Feb 5, 2026 78
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ ለዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ምርጫ እውን መሆን የመገናኛ ብዙሃን ኃላፊነት ድርብ መሆኑን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24/2018 ዓም ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅቶች እያደረገ ሲሆን የዕጩዎች ምዝገባም እየተከናወነ ይገኛል። በመጪው ጠቅላላ ምርጫ የመገናኛ ብዙሃን ድርሻን አስመልክቶ ኢዜአ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ትምህርት ክፍል መምህራንን አነጋግሯል። በዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ ተሻለ ተገኔ(ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በንቃት እንዲሳተፉ መገናኛ ብዙሃን ትክክለኛ መረጃ በመስጠት የምርጫ ህጉን በተመለከተ ግንዛቤ ማሳደግ ላይ ትኩረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።   በምርጫ ወቅት መራጮች በበቂ መረጃ ላይ ተመስርተው ድምጽ እንዲሰጡ የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም አክለዋል። የምርጫው ሂደት ትክክለኛ፣ ዴሞክራሲያዊና አካታች መሆኑን በመከታተልና የተቀመጡ የስነ ምግባር መርሆዎችን ተከትሎ መረጃ በመስጠት ህዝቡ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ ይገባቸዋል ነው ያሉት። የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ሂደቱን በመከታተል ለመራጩ ህዝብ ግንዛቤ በመፍጠር ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ በሚበጅ መልኩ አበክረው መስራት እንዳለባቸውም ጠቅሰዋል።   ምርጫው ተዓማኒ እንዲሆን የመገናኛ ብዙሃን ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የህዝብ ግንኙነትና ስነ ተግባቦት ትምህርት ክፍል ኃላፊና መምህር ወገኔ ዳንኤል ናቸው። መገናኛ ብዙሃን እና የሚዲያ ባለሙያዎች በምርጫ ዘገባ ወቅት ሙያዊ የስነ ምግባር መርሆዎችን ተከትለው የመስራት ግዴታ እንዳለባቸውም ነው ያመለከቱት።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየሰራን ነው - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Feb 5, 2026 60
ሐረር፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየሰሠሩ መሆኑን በሐረሪ ክልል በምርጫው የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከትናንት በስቲያ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የመንግስትን የ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ጊዜ መንግስት ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ፣ አካታች እንዲሁም ከባለፈው ምርጫ በሁሉም መስፈርት የተሻለ እንዲሆን አበክሮ እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። በሐረሪ ክልል የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እያደረጉት ያለውን ዝግጅት አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮዽያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ(ኢብአፓ) የሐረሪ ክልልና ድሬዳዋ አስተዳደር አስተባባሪ ሐሰነት ሙሜ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖለቲካ ምሕዳሩን ለማስፋትና የመድበለ-ፓርቲ ሥርዓትን ለማጠናከር የጋራ ምክር ቤት መመስረታቸውን አስታውሰዋል። የምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎች ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑንጠቁመው በዚህም ምክር ቤቱ 6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሚናውን ተጫውቷል ብለዋል። አክለውም ምክር ቤቱ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሕዝብ ዘንድ ተዓማኒነት ያለው እንዲሆን ለፓርቲ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከመስጠት ጀምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አመልክተዋል። ምክር ቤቱ አሁን ላይ 12 የፖለቲካ ፓርቲዎችን በአባልነት የያዘ ሲሆን በቀጣይ ሌሎች ፓርቲዎችንም የምክር ቤቱ አባል ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዳይሬክተር ሐሰን አብዲ 6ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከተደረጉ ምርጫዎች በተሻለ መልኩ አሳታፊ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህም ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የድርሻውን መወጣቱን አስታውሰዋል። አቶ ሐሰን አክለውም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም መመዘኛዎች ካለፉት ምርጫዎች በተሻለ አሳታፊ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢና የክልሉ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ(ነእፓ) ምክትል ሰብሳቢ አብዱልሃፊዝ አህመድ ፓርቲያቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።   ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለሀገሪቱ የዴሞክራሲ ግንባታ የድርሻቸውን ከሚወጡባቸው ጉዳዮች አንዱ ምርጫ እንደመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ሁሉን አሳታፊና ፍትሃዊ እንዲሆን የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ጥረት እያደረገ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
በመግባባት ላይ የተመሰረተ የምክክር ሂደት ማካሄድ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ መስጠት ነው
Feb 5, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ ብሔራዊ መግባባትን ለማጠናከር በመግባባት ላይ የተመሰረተ የምክክር ሂደት ማካሄድ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ መስጠት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።   በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ኮሚሽኑ በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የተከናወኑ ተግባራትን ገለፃ አድርገዋል። ኢትዮጵያ ያለፈችባቸው የግጭት አዙሪት የተሳሳቱ መንገዶች በሀገራዊ ምክክር መፍትሔ ሊያገኙ እንደሚገባ የዘመናት ጥያቄ ሆኖ መቆየቱን ተናግረዋል። ዘላቂ ብሔራዊ መግባባትን ለማምጣት ምክክር አስፈላጊ ነው ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፥ ምክክርም በመግባባት ላይ የተመሰረተ ሂደትን የሚፈልግ ጉዳይ ነው ብለዋል። በዚህም የአማራ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ መካሄዱን ገልጸዋል። የነፍጥ ትግል አሸናፊና ተሸናፊን የሚፈጥር እንጂ ሀገራዊ መግባባትን የሚያሰፍን እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ታጣቂ ኃይል የትጥቅ ትግልን አስከፊነት በቅጡ በመገንዘብ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ ይሰጣል ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፥ አጀንዳዎችን በመለየት በምክክር መፍትሔ ያገኛሉ በሚል ለወሰዱት ቁርጠኛ አቋም ምስጋና አቅርበዋል። የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበርና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ፥ የትጥቅ ትግል ህዝብን ከማጎሳቆል ያለፈ ፋይዳ እንደሌለው በመገንዘብ የሰላም ስምምነት መውሰዳቸውን አስታውሰዋል። በዚህም ለትጥቅ ትግል መነሻ የነበሩ ጉዳዮችን በመሰነድ ለአማራ ህዝብና ኢትዮጵያ ችግር የሆኑ አጀንዳዎች በምክክር መፍትሔ እንደሚያገኙ በማመን ለይተው ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል። በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የእስካሁኑ ክንውኖች የተደረገላቸው ገለፃም በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል ሂደቶችን እንዳለፈ መገንዘባቸውን ተናግረዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፥ የሶስት ዓመታት የትጥቅ ትግላቸውን በሚገባ በማጤን አሉኝ የሚሏቸውን ጉዳዮች በሰላማዊ መንገድ መፍትሔ ለማስገኘት የሰላም አማራጭን እንደተከተሉ ገልጸዋል።   የተሳሳተ ትርክት፣ የሕገመንግስት እና ተያያዥ ጉዳዮች የተካተቱባቸውን አጀንዳዎች በማደራጀት በጋራ የምክክር መድረክ መግባባትን በመፍጠር በሂደት መፍትሔ እንደሚያገኙ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር እያሱ አባተ፥ ከመንግስት ጋር ከደረሱት የሰላም ስምምነት በተጨማሪ አሉኝ የሚሏቸውንና እንዲፈቱ የሚፈልጓቸውን የተቆጠሩ አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል። ዓመታትን በተሻገረው የግጭት ቆይታቸው ህዝብን ከማጎሳቆል የዘለለ ፋይዳ እንዳልሰጠ ገልጸዋል። በቀጣይም በሰላማዊ አማራጭ ለህዝብ ተጠቃሚነትና ኢትዮጵያ ህልውና በሚበጁ ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ሌሎች በጫካ የሚገኙ ቀሪ ታጣቂዎችም የሰላም አማራጭን በመከተል ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ የመከላከያ የጋራ ኮሚቴ ስብሰባ በስኬት ተጠናቀቀ
Feb 5, 2026 56
የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ የመከላከያ የጋራ ኮሚቴ ስብሰባ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያና ኬንያ የመከላከያ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው 1ኛ መደበኛ የኢትዮ-ኬንያ የመከላከያ የጋራ ኮሚቴ ስብሰባ በስኬት ተጠናቋል። በመተማመን፣ በመከባበርና በጋራ ጥቅም መርህ ላይ የተመሰረተው የኢትዮጵያ እና የኬንያ መከላከያ የሁለትዮሽ ግንኙነት የሁለቱን ሀገራት ጥቅም የሚያስጠብቅ መሆኑን የኢትዮጵያን መከላከያ ልዑክ የመሩት የመከላከያ የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬከተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ ገልፀዋል።   ሜጄር ጄኔራል ተሾመ በውይይቱ ወቅት የቀረቡ አጀንዳዎች የሁለቱን ሀገራት የአጋርነትና የአብሮነት ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ከመሆናቸውም በላይ የቀጣናው አሁናዊ ሁኔታ የሚጠይቀውን የጋራ ተሳትፎ አስመልክቶ ጠንካራ አቋም እንዲያዝ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን አንስተዋል ብለዋል። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በጠንካራ የሁለትዮሽ ትብብራችንና ውጤታማነታችን በማያስደስታቸው አካላት እኩይ ተግባር ሳንዘናጋ የየበኩላችንን መወጣት አለብን ሲሉም ተናግረዋል።   ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ መከላከያ የበኩሉን ድርሻ በተመለከተ በኃላፊነት ስሜት፣ በትጋትና በውጤታማነት መወጣት የሚያስችል የላቀ ዝግጁነት እንዳለውም አረጋግጠዋል። የኬንያ የመከላከያ ኦፕሬሽን፣ ኢንዶክትሪኔሽን እና ስልጠና ኃላፊ ሜጀር ጄኔራል ሉዋሬ በበኩላቸው፤ ሁለቱ ሀገራት ለዘመናት የቆየ ጠንካራ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ያላቸው ከመሆናቸው በላይ በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በኢነርጂ ዘርፍ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው አስረድተዋል።     ይህ መድረክ የሁለቱን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ የሰላም እና ጸጥታ ዘርፎች የሚደረገውን ግንኙነት እና ትብብር በማጠናከር በኩል ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ማህበራዊ
ማህበሩ በደቡብ ሶዶ ወረዳ ከ284 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ያስገነባቸው የልማት ፕሮጀክቶች ስራ ጀመሩ
Feb 5, 2026 40
ወልቂጤ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር በምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ ከ284 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ያስገነባቸው የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት መስጠት ጀመሩ።   የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የልማት ማህበሩ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሙስጠፋ ሃሰን፤ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንዳሉት ማህበሩ የማህበረሰቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት የሚደረጉ ጥረቶችን እያገዘ ነው።   በተለይም መንግስት እያካሔዳቸው ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራትን በማገዝ ስኬታማ ስራዎች እየሰራ መሆኑንም ነው የጠቀሱት። ከዚህ ውስጥም ከ284 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ግንባታቸው ተጠናቆ ወደ አገልግሎት የገቡ የልማት ስራዎችን በዛሬው እለት ለማሕበረሰቡ ማስረከቡን አብራርተዋል። ማሕበሩ በንፁህ መጠጥ ውሃ፣ በጤና እና ትምህርት የመሰረተ ልማት ተደራሽነት ላይ የሚያከናውናቸው ተግባራትን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው የተናገሩት።   የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር ዋና ዳይሬክተር አቶ ቅባቱ ተሰማ በበኩላቸው፤ ማህበሩ የአርሶ አደሩን ኑሮ በሚያሻሽሉ ተግባራት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል። በግብርና፣ በትምህርት፣ በጤናና ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች ላይ እየሰራ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ ለአብነትም ባለፉት አምስት አመታት ውስጥ በደቡብ ሶዶ ወረዳ 140 የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የአካባቢው ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።   በትምህርትና በጤና እንዲሁም የግብርና ስራዎችን በማዘመንና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚከናወኑ ተግባራት ለማገዝ ማህበሩ ቁርጠኛ መሆኑንም አስረድተዋል። በቀጣይም ማህበሩ የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚደረጉ ተግባራትን ከማገዝ አንፃር የበኩሉን እንደሚወጣም ነው የጠቀሱት።   ማህበሩ ባስገነባው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና የጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የአካባቢው ነዋሪዎች አቶ አስናቀ ጉግሳ እና አቶ ይርጋለም ቁምቢ ናቸው። የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር በ2001 ዓ.ም መቋቋሙ ይታወቃል።
ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ሥርጭት ለመግታት ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ ነው 
Feb 5, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ሥርጭት ለመግታት ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢንዶክሬይንና ሜታቦሊዝም ማህበር ጋር በመተባበር አራተኛውን ዓመታዊ የጤና ጉባኤ አካሂዷል፡፡ በጉባኤው ላይ ጤና ሚኒስቴርን ወክለው የተገኙት በጤና ሚኒስቴር ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል ባለሙያ ዶክተር ሙሴ ገብረሚካኤል እንደገለጹት፤ የስኳር ሕመም መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት ከሰጠባቸው ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መካከል ቀዳሚው ነው ብለዋል።   የስኳር ሕመም ከመከሰቱ በፊት የአመጋገብ ሥርዓትን በማስተካከልና አካላዊ እንቅስቃሴ በማድረግ በቀላሉ መከላከል እንደሚቻል ተናግረዋል። በሀገራዊ ለውጡ መንግሥት የበሽታውን ሥርጭት ለመቆጣጠር የቅድመ መከላከል፣ የሕክምና አገልግሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ያካተተ ስትራቴጂ ቀርፆ ወደ ተግባር መግባቱንም ነው የገለጹት፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ዶክተር አህመድ ረጃ በበኩላቸው፤ ማህበሩ ጥቂት ባለሙያዎችን ይዞ የተመሠረተ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የባለሙያዎቹ ቁጥር እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።   እስካሁን በዘርፉ ለተሰማሩ ከ600 በላይ የጤና ባለሙያዎች ሥልጠና መሰጠቱን ጠቅሰው፤ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የስኳር፣ የታይሮይድና የሆርሞን ሕመሞች ዙሪያ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል። በቀጣይም ማህበሩ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ድርጅቶች ጋር ያለውን ቅንጅት በማጠናከር ክፍተቶችን ለመሙላት በትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
ኢንስቲትዩቱን የልህቀት ማእከል ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት ይጠናከራሉ   
Feb 5, 2026 60
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩትን አቅምና አደረጃጀት በማጎልበት የልህቀት ማእከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ገለጹ። የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት የሪፎርም፣ የአዲስ ሎጎ ማስተዋወቂያና በፍትህ ዘርፉ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለሙያዎችና አመራሮች እውቅና የመስጠት መርሃግብር የፍትህ ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል። በመርሃግብሩ ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ በአዲስ አደረጃጀት ወደ ስራ ገብቷል።   ኢንስቲትዩቱ ተጠሪነቱ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መደረጉ የምርምርና የስልጠና ስራዎች ከፍትህ አካላት ጋር በተጣጣመና በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል ያስችላል ብለዋል። አደረጃጀቱ የተቋሙን አገልግሎት ለማሻሻልና ለማቀላጠፍ እንዲሁም የህግ አወጣጥና አፈጻጸም ችግሮችን ለመፍታት የተቋሙን አቅም የሚያጠናክር ነው ብለዋል። የኢንስቲትዩቱን የአቅም ግንባታ፣ የምርምርና የመረጃ ማእከል ስራዎችን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት አዲስ ሎጎ ይፋ የተደረገ ሲሆን ይህም የኢንስቲትዩቱን የልህቀት ማዕከልነት ለማጎልበት ከሚከናወኑ ስራዎች ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል።   የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አበባ እምቢያለ በበኩላቸው፤ የኢንስቲትዩቱና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትብብር ማእቀፍ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።   ይህም በፍትህ ሰርዓቱ የሚከናወኑ የለውጥ ስራዎች ጠንካራ የምርምርና የፖሊሲ መሰረት እንዲኖራቸውና ኢንስቲትዩቱን የልህቀት ማእከል ለማድረግ የሚከናወኑ ስራዎች ላይ ጉልህ ሚና ያለው በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ መዋቅራዊ ተግዳሮቶችን በመፍታት ወደ ሁሉ አቀፍ የለውጥ ምእራፍ ተሸጋግሯል ።   የሶስት አመታት ፍኖተ ካርታና ስትራቴጂክ እቅድ ተዘጋጅቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በኢንስቲትዩቱ ከ80 በላይ ጥናቶችና ምርምሮች መካሄዳቸውን ገልጸው፤ በፍትሐብሔር ፣ በወንጀል ፣ባህላዊ ፍትህ አስተዳደር ፣ ሰብአዊ መብትና ሌሎች ጉዳዮች ለይ ምርምር ከተከናወነባቸው ጉዳዮች መካከል ለአብነት ጠቅሰዋል። ባለፉት ዓመታት ከ25 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የፍትህ ዘርፍ ባለሙያዎችና አመራሮች ስልጠና መሰጠቱንም አክለዋል። ኢንስቲትዩቱ ዘመኑ የሚጠይቀውን የእውቀት፣ የክህሎትና የቴክኖሎጂ የልህቀት ማእከል ለመሆን እየሰራ ነው ብለዋል። የስልጠና ማእከሉን ምቹ የማድረግ ፣ የኢ-ለርኒንግ ስቱዲዮ የማዘጋጀት ፣ የመረጃ ማእከል የማደራጀት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።
ኢኮኖሚ
መንግስት የህዝብን የልማት ጥያቄ እየመለሰ ነው -  አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Feb 5, 2026 69
ሻኪሶ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት የህዝብን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ እንደሚገኝ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ፡፡ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ድጋፍ የሚገነባው የሻኪሶ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተገኙበት የግንባታ ስራ ተጀምሯል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት መንግስት የህዝብን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡   ዛሬ የግንባታ ስራው የተጀመረው የሻኪሶ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክትም አካባቢው በቡና፣ በማዕድናትና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የአውሮፕላን ማረፊያው መገንባት የአካባቢውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያሳልጥ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አካባቢውን ለማልማት ላደረገው ዕገዛ ያመሰገኑት አቶ ሽመልስ፤ የአውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክቱን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ርብርብ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፤ አየር መንገዱ አዲስ አበባን ከሀገር ውስጥ ከተሞች ጋር የሚያገናኙ በርካታ በረራዎች እንዳሉት ጠቁመዋል።   የሻኪሶ አውሮፕላን ማረፊያም ተጨማሪ የአየር መንገዱ መዳረሻ በማድረግ የጉጂ ዞን የተፈጥሮ ሀብትን ለማልማት ተደማሪ አቅም እንደሚሆን አስረድተዋል። ፕሮጀክቱ ተጠናቆ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ሲጀመር የአካባቢውን ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማቀላጠፍና የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ የራሱ ድርሻ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው፤ ከዚህ በፊት በስፍራው የአውሮፕላን መንደርደሪያ እንደነበር አስታውሰው የክልሉ መንግስት የአውሮፕላን መንደርደሪያውን ወደ ንግድ አውሮፕላን ማረፊያነት ለመቀየር ያቀረበውን ጥሪ በመቀበል ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ግንባታውን ማስጀመሩን ገልፀዋል፡፡   ፕሮጀክቱ ተጠናቆ በተያዘለት ጊዜ አገልግሎት እንዲጀምርም የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡ የሻኪሶ አውሮፕላን ማረፊያ በ124 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሚገነባ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ በይፋዊ የግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የፌዴራል፣ የክልልና የጉጂ ዞን አመራሮች እንዲሁም አባገዳዎች ተገኝተዋል፡፡
በቡና ዘርፍ የተከናወኑ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለውጭ ምንዛሬ ገቢ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል
Feb 5, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ በቡና ዘርፍ የተከናወኑ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለውጭ ምንዛሬ ገቢ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ከምስራቅ አፍሪካ ፋይን ኮፊ ማህበር (AFCA) ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 22ኛው የአፍሪካ ፋይን ኮፊ (Africa Fine Coffee) ኤግዚቢሽንና ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።   ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በጀመረው በዚህ መድረክ ላይ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፣ የዘርፉ ተመራማሪዎችና ዓለም አቀፍ እንግዶች ተገኝተዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት 469ሺህ ቶን ቡና ለዓለም ገበያ በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን ገልጸዋል፡፡ ይህ ውጤት በሀገሪቱ የቡና ታሪክ ከፍተኛው የገቢና የጥራት መጠን ሆኖ መመዝገቡን ጠቅሰው፤ በያዝነው ዓመት የሚገኘውን ገቢ ወደ 3 ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለቡና ዘርፉ ዕድገት ትልቅ ድርሻ ማበርከቱንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ካለው የዓረቢካ ቡና ዝርያ 90 በመቶ የሚሆነውን የጄኔቲክ ብዝሃ-ህይወት በመያዟ ለዓለም የቡና ኢንዱስትሪ እንደ ዘር ባንክ እንደምትቆጠርም ተናግረዋል፡፡ ይህም ለተለዋዋጭ የአየር ንብረት የማይበገሩ ዝርያዎችን ለማምረት ልዩ ዕድል መፍጠሩን ተናግረው፤ ጥሬ ቡናን ከመላክ ባለፈ እሴት የተጨመረበት ቡናን ወደ ውጭ ለመላክ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና አማካኝነት በአህጉሪቱ ውስጥ የቡና ንግድን ለማጠናከር የፖሊሲ ማሻሻያዎች እየተደረጉ መሆናቸውንም እንዲሁ፡፡ የቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሻፊ ዑመር፤ መንግስት በቡናው ዘርፍ የጀመረው የሪፎርም ስራ አስደናቂ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል።   ይህ የለውጥ እርምጃ ከአምራች አርሶ አደሩ ጀምሮ በንግድ ሰንሰለቱ ውስጥ ያሉ አካላትን ተጠቃሚነት በእጅጉ ማሳደጉን ገልጸዋል። እየተካሄደ የሚገኘው ጉባኤ አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ተጠቅማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የቡና ገበያ ድርሻ እንድታሳድግ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር አስገንዝበዋል። የአፍካ (AFCA) ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ጊልበርት ጋታሊ በዚሁ ጊዜ በአፍሪካ የቡና ዘርፍን ለማዘመንና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን ለማረጋገጥ ከአጋር ድርጅቶች ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።‎   በተጨማሪም ለላኪዎች፣ ለገዢዎች፣ ለማሽን አምራቾች፣ ለቡና ጥራት ባለሙያዎች እና በጥቅሉ በዘርፉ ኢንዱስትሪው የአቅርቦትና የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ላሉ አካላት ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ኤግዚቢሽንና ኮንፍረንሱ ከዘርፉ ተዋናዮች ጋር ጠንካራ ትስስር በመፍጠር የአፍሪካን የቡና ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ትልቅ አቅም እንደሚሆን አመልክተዋል።
የግብርና ዘርፉን በማዘመንና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት ለመውጣት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Feb 5, 2026 49
ወላይታ ሶዶ ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ የግብርና ዘርፉን በማዘመንና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት ለመውጣት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የግብርና ግብዓት ስርጭትን አስመልክቶ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል።   በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ የሺእመቤት ነጋሽ፤ የግብርና ዘርፉን በማዘመንና ሜካናይዜሽንን ከማስፋት ባለፈ የግብአት አቅርቦቶችን በማሟላት ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ግብን ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። ኮርፖሬሽኑ ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ እንዲሁም ሌሎች ግብአቶችን በብዛትና በጥራት በማቅረብ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም መሰረት በበጀት ዓመቱ 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ለማቅረብ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። እስከአሁኑ ሂደት 560 ሺህ ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ለተጠቃሚዎች መድረሱን ጠቅሰው በዘርፉ ልማት የተያዘውን ግብ ለማሳካት በተደመረ አቅም መስራቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ለምርጥ ዘር አቅርቦትም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የግብርና ግብዓት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ፤ ኮርፖሬሽኑ የሚያቀርበው ግብዓት በክልሉ የግብርና ሴክተር የተያዘውን ግብ ለማሳካት ትልቅ አቅም መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ለዘርፉ ልማት ስኬታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራትና ውጤት ማምጣት ይጠበቅበታል ብለዋል።   በኦሮሚያ ክልል ግብርና ግብዓቶች ምርት ጥራትና ቁጥጥር የሻሸመኔ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚደቅሳ ጀቤሳ፤ በኮርፖሬሽኑ በኩል የግብዓት ስርጭት መኖሩ በጥራትና ምርታማነት ላይ ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ከኮርፖሬሽኑ ጋር ባለ ጠንካራ የትብብር ግንኙነት የዘር ጥራት ቁጥጥር በማድረግ የተሻለ ውጤት ማምጣት መቻሉን አንስተው በዚህም የአርሶ አደሩ ምርትና ምርታማነት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።  
የሌማት ትሩፋት መንግስት ለዜጋ እና ለሀገር ያለውን ክብር ያሳየበት ልዩ እሳቤ እና ትግበራ ነው
Feb 5, 2026 52
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018 (ኢዜአ)፡-የሌማት ትሩፋት መንግስት ለዜጋ እና ለሀገር ያለውን ክብር ያሳየበት ልዩ እሳቤ እና ትግበራ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ መንግስት በሌማት ትሩፋት ዘላቂ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ፖሊሲ ትግበራ ተደማሪ አቅም በማድረግ ሰርቷል ብለዋል፡፡   በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምዕናብ ልህቀት ፈልቆ የተጀመረው ኢኒሼቲቭ የብዙ ቤተሰብን ሕይወት ቀይሯል፣ ደግሞም ወደፊትም መቀየሩን ይቀጥላልም ሲሉ ጠቁመዋል፡፡ የሌማት ትሩፋት ለዘመናት ጸጋ ሆነው ያልታዩ ጓሮዎችን የልማት ከባቢ አድርጓል፡፡ በመሆኑም የተመጣጠነ ምግብ በሽታ መከላከልን ካስቀደመው የጤና ፖሊሲያችን ጋር ግንኙነቱ ቀጥተኛ ነው፡፡ በዚህም የመደመር እሳቤ ባፈለቀው የፈጠራ ተግባር የእንስሳት ተዋጽኦ በአግባቡ ወደ ሌማታችን አምጥቷል፡፡   የሌማት ትሩፋት የተሳሰረው ከከበረ የሰዎች ከሕይወት እና ጤና እንዲሁም ከትልቁ የሃገር መልክ እና ክብር ብሎም ከዘላቂ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ርዕያችን ጋር ነው ያሉት አቶ ተመስገን፥ በትጋት የሚሰሩ ክንዶች ሌማታቸውን አትረፍርፈዋል ወደፊትም ያትረፈርፋሉ በማለት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ማዕከሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ይደርስ የነበረውን መጉላላት አስቀርቷል
Feb 5, 2026 27
ባህር ዳር፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ ባህርዳር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ቀደም ሲል ይደርስ የነበረውን መጉላላት እንዳስቀረላቸው ተገልጋዮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትናንት በስቲያ በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ጊዜ ከመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራርያ፣ አገልግሎቱ የተጀመረበት ጊዜ አጭር ቢሆንም በዘርፉ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለና በቀጣይም የአገልግሎቱን ተደራሽነት ለማስፋት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።   ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር ቀደም ሲል ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት እንዳስቀረላቸው ገልጸዋል። ከማዕከሉ ተገልጋዮች መካከል አንዷለም ሞላ አንዱ ነው። እርሱ እንደሚለው፣ቀደም ሲል የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደ ክፍለ ከተማና ቀበሌ ሲሄድ ጉዳዩ ሳይፈጸም ተደጋጋሚ ቀጠሮ ብቻ ይሰጠው ነበር።   መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር የሚፈልገውን አገልግሎት በፍጥነት ማግኘት እንዳስቻለው ገልጿል።። ሌላው የማዕከሉ ተገልጋይ አታለል ሙሴ በአንድ ቦታ ላይ በቴክኖሎጂ የታገዘ በርካታ አገልግሎቶችን በማግኘቱ ጊዜውንና ወጪውን እንደቆጠበለት ተናግሯል።   አገልግሎቱ ቀደም ሲል ሲነሳ የነበረውን የመልካም አስተዳደርና የብልሹ አሰራር ችግሮችን በመፍታት ለተገልጋዩ እፎይታ የሰጠ መሆኑንም አመልክቷል። በማዕከሉ የሚፈልጉትን አገልግሎት በፍጥነት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላዋ ተጋልጋይ አለሚቱ ንጉሴ ናቸው።   እንዲህ አይነት አገልግሎቶች መጉላላትን በመቀነስ የህዝብን እርካታ የሚጨምሩ በመሆናቸው በሁሉም አካባቢዎች ሊሰፉ ይገባልም ብለዋል። የባህር ዳር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስተባባሪ ማስረሻ ፈንታ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ የ12 ተቋማት 65 አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ ታግዘው እየተሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። በማዕከሉ እየተሰጡ ከሚገኙ አገልግሎቶች መካከል የባንክ፣ የኢትዮ-ቴሌኮም፣ የትራንስፖርት፣ የመሬት ጉዳዮች፣ የንግድና የውሃና ፍሳሽ ይገኙበታል ብለዋል።   የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት መምሪያ ሃላፊ ጤናው ምህረቱ፤ ቀደም ሲል ሕብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ በርካታ ቅሬታዎች ሲያነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ በፍጥነትና በጥራት መስጠት መጀመሩ የተገልጋዮችን እንግልት በማስቀረት ቅሬታውን ፈቷል ብለዋል።   ማዕከሉ አሁን ለይ በቀን 325 ያህል ተገልጋዮችን እያስተናገደ መሆኑን ጠቅሰው፣ በቀጣይም አገልግሎቱን ለማስፋት ጥረት ይደረጋል ብለዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እተደረገ እንደሚገኝም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መግለጻቸው ይታወሳል።  
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሊያሸጋግር ነው
Feb 5, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፦ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሊያሸጋግር መሆኑን አስታወቀ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት ጋር አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ለማሸጋገር የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።   ስምምነቱን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ጋር ተፈራርመዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ተቋማትን ወደ ዘመናዊ አሰራር ለማሸጋገር ጉዞ ጀምራለች። የፕላንና ልማት ሚኒስቴርም አሰራሩን ወደ ዲጂታል ለማሸጋገር ግብ ይዞ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬው ስምምነትም የዚሁ አካል ነው ብለዋል።   ስምምነቱ ሀገራዊ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ የልማት ስራዎች በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆናቸውን በዘመናዊ አሰራር ለመከታተል እና ለማረጋገጥ የዲጂታል ስርዓት መዘርጋት የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል። የልማት አስተዳደር ስራዎችና ፖሊሲዎች የሚያመጡትን ውጤት በትክክለኛ መረጃ ተመስርቶ ግምገማ ለማድረግ ትልቅ መሰረት የሚጥል መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡   የጥቅል አገራዊ ምርት ዕድገት እና ጥራትን ለመመዘንም ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል ብለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዮት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መረጃን ተንትኖ ስራ ላይ ማዋል ዘመናዊ መሰረተ ልማት የሚጠይቅ መሆኑን ጠቁመዋል።   በመሰል ስራ ላይ የተሰማራው ፕላንና ልማት ሚኒስቴር ስራው እንዲሳለጥ ፕሮጀክቱን ከተቀመጠው ጊዜ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ርብርብ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። ለዚህም የሁለቱም ተቋማት የቴክኒክ ኮሚቴ በጋራ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
ፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ሴቶች በዲጂታል ኢኮኖሚው ውስጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስቻይ ሁኔታን ፈጥሯል
Feb 5, 2026 44
ጎንደር ፤ጥር 28/2018(ኢዜአ)፡- ፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የብድር አገልግሎትና የስራ እድል ተጠቃሚ እንድንሆን አስቻይ ሁኔታን ፈጥሮልናል ሲሉ በጎንደር ከተማ የሚገኙ ሴቶች ገለጹ፡፡ ባለፉት ስድስት ወራት ከ183 ሺህ በላይ ሴቶች የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ማውጣታቸውን የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ እታገኝ ፈጠነ፤ የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ማውጣቴ በተለያዩ መስኮች ተጠቃሚ ለመሆን አስችሎኛል ነው ያሉት። ከዚህ ውስጥም ብድር በማግኘት የግል ስራቸውን ለማከናወን ከመቻላቸውም ባለፈ በመንግስት ተቋማትም ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ነው የሚያስረዱት፡፡ ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ቸርነት ጌታቸው በበኩላቸው የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ አካል ጉዳተኞች የመንግስት አገልግሎትን ለማግኘት ይገጥመን የነበረውን እንግልትና ውጣ ውረድ ያስቀረ ነው ብለዋል፡፡ መታወቂያውን በማውጣትና የአካል ጉዳተኞችን በማህበር በመደራጀታችን ከከተማ አስተዳደሩ የመስሪያ ቦታና የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ በመሆን ወደ ስራ ገብተናል ሲሉ ገልጸዋል። የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ የዜግነት ማረጋገጫ ከመሆን ባለፈ ሴቶች በሁሉም ዘርፍ እኩል ተጠቃሚና ተሳታፊ እንዲሆኑ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከቱን የገለጹት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ብርቱካን ብርሃኑ ናቸው፡፡ በተለይም ሴቶች ያለ ንብረት ማስያዣ ከፋይናንስ ተቋማት የብድር አገልግሎት እንዲያገኙ መልካም እድሎችን በመፍጠሩ የብድር አገልግሎት አግኝተው የግል ስራቸውን ለማከናወን እንደቻሉ ተናግረዋል፡፡ በጎንደር ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የሴቶች ንቅናቄና ተሳትፎ ማስፋፊያ ቡድን መሪ አቶ ተከታይ ጫቅሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከ183 ሺህ በላይ ሴቶች ፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ወስደዋል ነው ያሉት። ያለፉት ስድስት ወራት አፈፃፀም በእቅድ ከተያዘው በ10 ሺህ ብልጫ ማሳየቱን ጠቁመው አስከ በበጀት ዓመቱ ማጠቃለያም ከ242 ሺህ በላይ ሚሆኑ ሴቶች የፋይዳ መታወቂያን እንዲያወጡ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን ለፓርላማ አባላት በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ በሌሎች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራ ከአፍሪካ ግንባር ቀደም መሆኗን መናገራቸው ይታወሳል።  
በክልሉ የልማት ሥራዎችን በውጤታማነት ለመፈጸም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወሳኝ ሚናን ይጫወታል
Feb 5, 2026 85
ባህርዳር፤ ጥር 28/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የልማት ሥራዎችን በውጤታማነት ለመፈጸም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወሳኝ ሚናን እንደሚጫወት በምክትል ርዕስ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ በክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ የተዘጋጁ የፕሮጀክት አስተዳደር ሥርዓት (PMS) እና የቁልፍ ተግባራት አፈፃፀም አመላካቾች (KPI) መተግበሪያዎች ስራ ማስጀመሪያ መድረክ በባህር ዳር ከተማ መካሄድ ጀመረ።   በምክትል ርዕስ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፣ተለዋዋጭ በሆነው አለም ቴክኖሎጂን ማልማትና መጠቀም ወሳኝ ነው። በክልሉ የተያዙ የልማት ግቦችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ቴክኖሎጂ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል። ከዚህ አኳያ የፕሮጀክት አስተዳደር ሥርዓትን ለማሻሻልና የሀብት ብክነትን ለመከላከል የሚያስችሉ መተግበሪያዎች መበልጸጋቸውን ተናግረዋል። መተግበሪያዎቹ እንዲሁም የተቋማትን የተግባራት አፈፃፀም ጥንካሬና ድክመቶችን የሚያመላክቱ መሆናቸውንም አመልክተዋል። ክልሉ ቴክኖሎጂን በማልማትና በመጠቀም ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን ጥረት እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሚለሙ ቴክኖሎጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ብለዋል። የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ሃላፊ የቻለ ይግዛው በበኩላቸው፣ በክልሉ ያሉ ፀጋዎችን ለይቶና አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል ቴክኖሎጂ ሁነኛ አማራጭ መሆኑን ተናግረዋል።   እንደ ሀገር ለቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የዚህ ማሳያ ነው ብለዋል። ይፋ የተደረጉ መተግበሪያዎችም የፕሮጀክት አስተዳደር ስርዓትን በማዘመን ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲፈጸሙ ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚያስችል አመልክተዋል። የመንግስት የልማት ስራዎች በተቀመጠላቸው ዕቅድ መሰረት ተፈፃሚ እንዲሆኑ ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ ደመቀ ቦሩ (ዶ/ር) ናቸው።   በማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ፣ በፕሮጀክቶች አፈፃፀም፣ በግል ኢንቨስትመንትና የመረጃ ሥርዓት ዋና ዋና ቁልፍ ተግባራት ተለይተው ፍትሃዊነትን ለማስፈን እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የእነዚህ ቴክኖሎጂዎች ተግባራዊ መደረግ ተቋማትን በውጤት ለመለካት የሚያስችል ሲሆን ዕቅድና ሪፖርታቸውን በቴክኖሎጂ ታግዞ ለመከታተል እንደሚያግዝም ተናግረዋል። በመድረኩ የተቋማት ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ሲሆን የለሙት መተግበሪያዎች ቀርበው ውይይት እየተደረገ ይገኛል።        
ስፖርት
ነገሌ አርሲ መቀሌ 70 እንደርታን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ አደረገ 
Feb 5, 2026 24
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018 (ኢዜአ)፦‎ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገሌ አርሲ መቀሌ 70 እንደርታን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ርሆቦት ሰላሎ በ41ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። የመቀሌ 7ዐ እንደርታው ጋትሉዋክ ቱት በ62ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በሊጉ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ነገሌ አርሲ በ35 ነጥብ ደረጃውን ከአራተኛ ወደ ሶስተኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን አሳክቷል።   በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቀሌ 70 እንደርታ በ18 ነጥብ 17ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ተገኝቷል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ በተደረጉ የ18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ባህር ዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት አቻ ሲለያዩ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያ መድን እና ፋሲል ከነማ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጥሏል 
Feb 5, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2018 (ኢዜአ)፦‎ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ፍጹም ጥላሁን በ13ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ ቅዱስ ጊዮርጊስ መሪ ሆኗል። ይሁንና መሪነቱ የቆየው ለተወሰኑ ደቂቃዎች ነው። የቅዱስ ጊዮርጊሱ ጥዑመልሳን ኃይለሚካኤል በ16ኛው ደቂቃ በራሱ ላይ የወልዋሎን የአቻነት ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ፍሬው ሰለሞን ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ60ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ማስቆጠር አልቻለም። ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ24 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት አራት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ17 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ሶስት ነጥብ ማግኘት አልቻለም። በአሁኑ ሰዓት ነገሌ አርሲ ከመቀሌ 70 እንደርታ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የሐረማያ ሐይቅ የቱሪስት መዳረሻነት የማበልጸግ ስራ በተቀናጀ መንገድ በመከናወን ላይ ይገኛል
Feb 2, 2026 131
ሐረማያ ፤ጥር 25/2018 (ኢዜአ) ፡-የሐረማያ ሐይቅን የቱሪስት መዳረሻነቱን የማበልጸግ ስራ በተቀናጀ መልኩ እየተካሔደ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ። በማያ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙት የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል የሐረማያ ሃይቅ እንዱ ነው። ለበርካታ ዓመታት ደርቆ የነበረው ሐይቁ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች ትኩረት ተደርጎ በመከናወናቸው ወደ ቀድሞው ይዞታው መመለስ ችሏል። የከተማ አስተዳደሩ እና የአካባቢው ማህበረሰብ ሃይቁን እያለማውና እየተንከባከበው በመሆኑም የጎብኚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ጀሚላ ሲምቢሩ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ሐይቁ ከመዝናኛነቱ ባለፈ ለወጣቶች የስራ እድል እየፈጠረ የሚገኝ ሲሆን በዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የማጎልበት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። አካባቢው ትልልቅ እሴቶችና ጸጋዎች የሚገኙበትና በኪነ ጥበቡም ዘርፍ ስመ-ጥር አርቲስቶች የፈለቁበት መሆኑንም ይገልፃሉ። የአካባቢውን ባህል፣ ኪነ ጥበቡብና ቱሪዝሙ ዘርፉን እንደ አንድ ጸጋ በመጠቀምና ከቱሪዝም ጋር በማሰናሰል የዘርፉን ኢኮኖሚ ማሳደግና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።   የማያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢፍራህ ወዚር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በአፈርና ውሃ ጥበቃ እና በአረጓዴ አሻራ ስራ የተመለሰውን የሐረማያ ሃይቅ አጠቃቀምን የማስተካከል፣ የመጠበቅና የመንከባከብ ስራ እየተከናወነ ይገኛል። ሐይቁ ወደ ቀድሞ ቦታው መመለሱ ለጎብኚዎች እርካታን ከማጎናጸፉ ባለፈ ለአካባቢው ነዋሪዎችና ለወጣቶች የገቢ ምንጭ እየሆነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የሐረማያ ሐይቅ በተደረገለት እንክብካቤ ውብና ማራኪ የቱሪስት ቀልብ የሚስብ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፤ ለወጣቶችም የገቢ ምንጭ ማግኛ ሆኗል ያለው ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የቱሪዝም ባለሙያ ኦሊያድ በሪሶ ናቸው።   በአካባቢው ባለሀብቶችን በመጋበዝ ሎጆችና ሪዞርቶች በማስፋፋት የተሻሉ ስራዎችን መስራት እንደሚቻልም ነው አቶ ኦሊያድ አስተያየታቸውን የሰጡት።   በሐረማያ ሐይቅ ላይ የጀልባ አገልግሎት የሚሰጠው ወጣት ሙርቲ አህመድ፤ጎብኚዎችን በጀልባ ከማስጎብኘት ስራ በተጨማሪ በአሳ ልማት ስራም መሰማራቱን ይገልፃል።    
በአማራ ክልል የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ምርታማነት እንዲጎለብት አግዘዋል
Feb 2, 2026 175
‎ባህር ዳር፤ጥር 25/2018 (ኢዜአ)፡- አማራ ክልል የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነት እንዲጎለብት እገዛ ማድረጋቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ‎የቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት፤ ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነት እንዲያድግ አግዘዋል። ‎ስራውን በማስቀጠልም ‎በያዝነው የበጋ ወራት በተለዩ ዘጠኝ ሺህ 206 ተፋሰሶች በ456 ሺህ 411 ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ለማከናወን ግብ ተይዞ ወደ ተግባር ተገብቷል።   ‎እስካሁን በተደረገ ጥረትም የዕቅዱን 37 በመቶ ማከናወን እንደተቻለ ጠቅሰው፤ በዚህም ከ3 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልፀዋል። ‎ከዚሁ በተጓዳኝም ለመጪው ክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ የሚሆን ቦታ የመለየትና ለተከላ የሚውል ከ አንድ ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን አንስተዋል። በተቀናጀ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ ላይ ከተሰማሩ አርሶ አደሮች መካከል ‎በደቡብ ጎንደር ዞን የፋርጣ ወረዳ አርሶ አደር ዓለሙ መንጌ በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ከህልውና ጋር የተያያዘ መሆኑን በመረዳት ተግባሩን በማጠናከር በየዓመቱ በራሳቸው ተነሳሽነት እያከናወኑ መሆናችውን አንስተዋል። ‎ዘንድሮም በቀበሌያቸው በተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ላይ በንቃት በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በቀበሌያቸው ያከናወኑት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የመሬቱን ለምነት በመመለስ ለምርታማነት ማደግ አስተዋጽኦ እንዳበረከተላቸው የገለፁት ደግሞ ‎ሌላኛው የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ካሳሁን መንግስት ናቸው። ቀደም ሲል የተሰራው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ግማሽ ሄክታር የእርሻ ማሳቸውን ለምነት በመመለሱ እስከ አምስት ኩንታል ተጨማሪ ምርት እንዲያገኙ ማስቻሉን ገልፀዋል። የልማት ስራው ተጠቃሚነታቸውን በተጨባጭ እያሳደገ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ላይ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። ‎በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተከናወነ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራም የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባሻገር በግብርና ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ እንዳስቻለም ተመላክቷል።  
የአረንጓዴ አሻራ፣ የተፋሰስ ልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች የውሃ አዘል መሬቶችን ከመጠበቅ አኳያ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ ነው
Feb 2, 2026 152
አዲስ አበባ፤ ጥር 25/2018 (ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ፣ የተፋሰስ ልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች የውሃ አዘል መሬቶችን ከመጠበቅ አኳያ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ገለጸ፡፡ ባለስልጣኑ የዘንድሮውን የዓለም የውሃ አዘል መሬቶች ቀን "የውሃ አዘል መሬት እና ሀገር በቀል እውቀት፤ የባህል ቅርሳችንን እናክብር" በሚል መሪ ቃል እያከበረ ይገኛል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የተለያዩ የውሃ አዘል መሬቶች እና የብዝሃ ህይወት ባለቤት ናት።   እነዚህ ተፈጥሯዊ ጸጋዎች ተጠብቀው ለትውልድ እንዲሸጋገሩም ሀገር በቀል እውቀት እና ባህላዊ የጥበቃ ስልቶች ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የውሃ አዘል መሬቶች ከፍተኛ ጥቅም እያስገኙ መሆኑን ጠቁመው የተበከለ ውሃን በተፈጥሯዊ መንገድ ማጣራት፣ የጎርፍ አደጋን መከላከል እና የአፈር እርጥበትን መጠበቅ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም እና የአካባቢን ሙቀት መቀነስን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በእነዚህ ወሳኝ የተፈጥሮ ሃብቶች ላይ የሚደርሱ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ዘመናዊውን ሳይንሳዊ እውቀት ከሀገር በቀል ጥበብ ጋር አቀናጅቶ መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተተገበሩ ያሉ የአረንጓዴ አሻራ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች ለውሃ አዘል መሬቶች ደህንነት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን አረጋግጠዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ደን ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቴ ግጄ፤ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ ውሃ አዘል መሬቶችን የመለየትና ተገቢውን ጥበቃ የማድረግ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   የአማራ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ደን ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ በልስቲ ፈጠነ በበኩላቸው፤ በክልሉ የሚገኙ የውሃ አዘል ስፍራዎችን በዘላቂነት ለማልማት ዘመናዊ ሳይንሳዊ ዕውቀቶችን ከባህላዊ ጥበቃ ዘዴዎች ጋር በማቀናጀት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።   ማህበረሰቡ ስለ እርጥብ መሬቶች ፋይዳ ያለውን ግንዛቤ እንዲያሳድግና ከሀብቱ በሥርዓት ተጠቃሚ እንዲሆን ሰፊ የትምህርትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኦሮሚያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኢዳቲ ጠቁመዋል።
በዞኑ አርብቶ አደሩን በማሳተፍ ከ33 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው
Jan 31, 2026 176
ጂንካ፤ ጥር 23/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሩን በማሳተፍ ከ33 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የአፈርና ውሃ ጥበቃና የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ ምንላርገው አዲሱ፣ በዞኑ በተጀመረው የተፋሰስ ንቅናቄ ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት 50 ንዑስ ተፋሰሶች የማልማት ስራ እንዲሁም በአርብቶ አደርና በዝቅተኛ አካባቢዎች ደግሞ ከ17 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።   በአጠቃላይ በዞኑ ከ33 ሺህ ሄክታር መሬት የተፋሰስና የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፥ የተፋሰስ ልማቱ በተከናወነባቸው ስፍራዎች ከ11 ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተከላ ይከናወናል ነው ያሉት። በዘንድሮው ዓመት የተፋሰስ ልማት በሳይንሳዊ ጥናት የተደገፈ ስነ-አካላዊና ስነ-ህይወታዊ ስራዎች እንደሚከናወኑም ጠቁመዋል። ልማቱ የተከናወነባቸው አካባቢዎችን ከሰውና ከእንሰሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በዞኑ ሐመር ወረዳ እየተከናወነ ባለው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተሳተፉት ወይዘሮ አልጎ በሌ፥ በአካባቢው የቡስካ ጥብቅ ደን እንደሚገኝ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ደኑ በሰውና በእንስሳት ጉዳት ይደርስበት እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ደኑን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ የመጠበቅ ስራ ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። በአካባቢያችን የተፋሰስ ልማት ከተጀመረ ወዲህ አካባቢው ለእርሻ ተስማሚ መሆን ጀምሯል ያሉት አቶ አስ ኦቶሎ ለእንስሳት የሚሆን በቂ የግጦሽ ሳር የምናገኝበት ዕድልንም እየፈጠረ ነው ብለዋል።      
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ የምታስተናግዳቸው አህጉራዊ ሁነቶች
Feb 4, 2026 230
በሙሴ መለሰ የዓለም ስርዓት በፍጥነት እየተቀያየረ ይገኛል። አፍሪካ በዚህ ተለዋዋጭ ስርዓት ውስጥ የሚገባትን ቦታ የመያዝ ጉዳይ የመነጋገሪያ አጀንዳ ከሆነ ሰነባብቷል። አፍሪካ በርካታ ወጣት የያዘች እና ብዝሃ የተፈጥሮ ፀጋዎች ያሏት አህጉር ናት። በአፍሪካ ተግባራዊ የተደረገው አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በቀጣናው የንግድ ትስስርን በማሳለጥ እድገትን የማፋጠን ተስፋ ተጥሎበታል። አፍሪካ እድሎቿን በሚገባ ለመጠቀምና የሚስተዋሉ ፈተናዎቿን ለመሻገር ምላሽ የምትሰጥበት የልማት እና እድገት ጉዞዋን ከመበየን ባለፈ በዓለም መድረክ የሚኖራትን ሚናም ይወስናል። በአህጉር ደረጃ የተቀመጡ እንደ አጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ያሉ አህጉራዊ ማዕቀፎች እንዲሳኩ ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። መንግስታት፣ የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮች ትብብራቸው ማጠናከር ይኖርባቸዋል።   የተገቡ ቃልኪዳኖችን ወደ ሚለካ ውጤት ለመቀየር ዘላቂነት ያለው አመራር ሰጪነት፣ ኢንቨስትመንትን ማጠናከር እና ተከታታይነት ያለው ውይይቶችን ማድረግ ይገባል። ውሳኔ ሰጪዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኙ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ መድረኮች በአጀንዳዎች ላይ የተቀናጀ የተግበባር ምላሽ ለመስጠት ቁልፍ ሚና አላቸው። አፍሪካ እድሎቿን በመጠቀም እና ፈተናዎቿን በማለፍ መንገድ ላይ በሆነችበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ ሁለት ወሳኝ አህጉራዊ ሁነቶችን ታስተናግዳለች። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የመሪዎች ጉባኤ መሪ ሀሳብ ነው።   ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። የመሪዎች ጉባኤው በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ያስተላልፋል ተብሎም ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ኮሚቴ ተወካዮች (PRC) ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ መክሯል።   ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን አቅርቧል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። ከአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ማግስት ሌላኛው በኢትዮጵያ የሚካሄደው ዘጠነኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ነው። የቢዝነስ ፎረሙ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(ኢሴኤ) ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሁነቱን አዘጋጅተውታል። “የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ በፋይናንስ መደገፍ፤ ስራ እና ኢኖቬሽን ለዘላቂ ትራንስፎርሜሽን” የፎረሙ መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም በአፍሪካ የልማት እና የኢኮኖሚ እድገት ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን በማድረግ በየዓመቱ የሚካሄድ ከፍተኛ አህጉራዊ የምክክር መድረክ መሆኑን የኢሲኤ መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ አጋርነትና የኢንቨስትመንት መጠንን ማሳደግ በተለይም የመንግስት እና የግል የተቀናጀ የፋይናንስ አቅርቦትን ጨምሮ የተለያዩ የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይወያያል። የወጣቶችን የኢኖቬሽን ስራ ከፋይናንስ አቅርቦት ጋር የሚያስተሳስር የአፍሪካ የወጣቶች አይበገሬነትና ትራንስፎርሜሽን ማዕቀፍ ይፋ ይሆናል። በኢሲኤ የበለጸገውና የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ ቃል ኪዳኖችን ትግበራ የሚከታታልና የሚቆጣጠር ስርዓትም በፎረሙ ይፋ ሆኖ ወደ ትግበራ ይገባል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው ሁነት ላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የምክክር መድረኮችና የባለሙያዎች ውይይቶች ይደረጋሉ።   አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጣራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ አውደ ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። ከአህጉራዊ ሁነቶቹ ባሻገር የባለብዙ ወገን መድረክ የሆነው የአፍሪካ እና ጣልያን ጉባኤ የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ሁነቶቹን ማዘጋጀቷ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ጸንቶ የቆየውን የመሪነት ሚናዋን እንዲሁም የአህጉራዊ ምክክር፣ የባለብዙ ወገን ውይይቶችና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባት ማዕከልነቷንም አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ በኮሪደር ልማት እና በከተማ ማዘመን ስራ በፍጥነት እየተለወጠች ሲሆን የሁነቱ ተሳታፊዎች ከስብሰባው ባለፈ የመዲናዋን አዲስ መልክ የመመልከት እድል ያገኛሉ። የእነዚህ አህጉራዊ ስብሰባዎች ስኬት የሚለካው በአቋም መግለጫ ሳይሆን አጋርነትን በማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና የሚጨበጥ ውጤት በአህጉሪቱ በማስመዝገብ ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ የምታዘጋጃቸው አህጉራዊ ሁነቶች አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጣራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ አውደ ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። ከአህጉራዊ ሁነቶቹ ባሻገር የባለብዙ ወገን መድረክ የሆነው የአፍሪካ እና ጣልያን ጉባኤ የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ሁነቶቹን ማዘጋጀቷ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ጸንቶ የቆየውን የመሪነት ሚናዋን እንዲሁም የአህጉራዊ ምክክር፣ የባለብዙ ወገን ውይይቶችና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባት ማዕከልነቷንም አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ በኮሪደር ልማት እና በከተማ ማዘመን ስራ በፍጥነት እየተለወጠች ሲሆን የሁነቱ ተሳታፊዎች ከስብሰባው ባለፈ የመዲናዋን አዲስ መልክ የመመልከት እድል ያገኛሉ። የእነዚህ አህጉራዊ ስብሰባዎች ስኬት የሚለካው በአቋም መግለጫ ሳይሆን አጋርነትን በማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና የሚጨበጥ ውጤት በአህጉሪቱ በማስመዝገብ ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ የምታዘጋጃቸው አህጉራዊ ሁነቶች አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች።
በኒጀር በደረሰ ጥቃት መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው የአስካይ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ተጠግነው በቅርቡ አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ
Feb 3, 2026 120
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦ በኒጀር ዋና ከተማ በደረሰ ጥቃት መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት የአስካይ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ተጠግነው በቅርቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ ፡፡ አየር መንገዱ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው ማብራሪያ ባለፈው ሐሙስ ጥር 21/ 2018 ዓ.ም ሌሊት በኒጀር ዋና ከተማ ኒያሚ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰው ጥቃት ሁለት የአስካይ አየር መንገድ ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ፡፡ አውሮፕላኖቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አጋር የሆነው የአስካይ አየር መንገድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት ከአውሮፕላን አከራዮች የተከራያቸው እና በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የተመዘገቡ መሆናቸውን አስረድቷል፡፡ በአውሮፕላኖቹ ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመገምገም የተላከው የቴክኒክ ቡድን ጉዳቱ መጠነኛ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን አውሮፕላኖቹ ተጠግነው በቅርቡ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡም ተገልጿል ::
የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም አጋርነታቸውን ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Feb 2, 2026 122
አዲስ አበባ፤ጥር 25/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም ሰላምና ልማትን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች አጋርነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር ጋር በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተወያይተዋል። ውይይቱ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ በቆየው የአፍሪካ እና ዩናይትድ ኪንግደም አጋርነት ያተኮረ ነው። ሁለቱ ወገኖች የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እና ህግን መሰረት ያደረገ ዓለም አቀፍ ስርዓት ለመጠበቅ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።   የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ዩናይትድ ኪንግደም ከአፍሪካ ጋር ያላትን የረጅም ጊዜ ትስስር ያደነቁ ሲሆን በዓለም ላይ ያላትን ገንቢ ሚና እና ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ጋር በጤና፣ ትምህርት፣ የአየር ንብረት ምላሽ እና ንግድ ያላትን ትብብር አንስተዋል። ሀገሪቷ ለአፍሪካ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) በአደጋ ጊዜ ዝግጁነት እና ምላሽ እንዲሁም በሶማሊያ ለአፍሪካ ህብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) ድጋፍ እያደረገች እንደምትገኝም አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር የአፍሪካ ህብረት በዓለም ዲፕሎማሲ፣ ቀጣናዊ ሰላም እና ልማት ያለውን ሚና አድንቀዋል። ሁለቱ ወገኖች የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም በሱዳን፣ በሳሄል ቀጣና እና በሶማሊያ ያለውን የአፍሪካ ህብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሀገራት ለውኃ አቅርቦት፣ ጥራት እና ለንጽህና መሰረተ ልማቶች ቅድሚያ መስጠት ይጠበቅባቸዋል
Feb 1, 2026 234
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ሁሉም ሀገራት ለውኃ አቅርቦት፣ ለጥራት እና ለንጽህና መሰረተ ልማቶች ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው የአፍሪካ ሕብረት አስገነዘበ። በሕብረቱ የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ጥበቃ ኮሚሽነር ሙሴ ቪላካቲ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አህጉራዊው የግብርና ልማት ፕሮግራም ባለፉት 20 ዓመታት በአባል ሀገራት ዘንድ ጉልህ ለውጦች ማምጣቱን ገልጸዋል።   ይህም አባል ሀገራት ጠንካራ የግብርና ዕቅድ ሥርዓት እንዲዘረጉ፣ ውጤታማ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም ቀረፃ እንዲኖራቸው እና በምርትና ምርታማነት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማገዙን አንስተዋል። ፕሮግራሙ ትኩረት የሚያደርገው በተለይም በምርት መጠንና በምርታማነት ዕድገት ላይ በመሆኑ፤ በአሁኑ ወቅት በበርካታ ሀገራት ውስጥ የሚታየው የምርት መጠን መጨመር የዚሁ ጥረት ውጤት ነው ብለዋል። ማንኛውም የልማት እንቅስቃሴ ከውኃ ጋር የተቆራኘ መሆኑን አስገንዝበው፤ ግብርናን፣ ኢነርጂን ወይም ጤናን ስናስብ ሁሉም ነገር ከውኃ ጋር የተያያዘ ነው፤ ስለዚህ ውኃ ለዘላቂ ልማት እጅግ ወሳኝ ነው ብለዋል።   ለዚህም ነው “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የሚለው መሪ ሐሳብ ለ39ኛው የሕብረቱ መሪዎች ጉባዔ የተመረጠው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ጉዳዩ በሕብረቱ አጀንዳነት የተያዘው በአህጉሪቱ ያለውን የውኃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል። በአህጉሪቱ ወደ 400 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች መሰረታዊ የውኃ አገልግሎት እንደማያገኙ ጠቁመው፤ ከ700 ሚሊየን የሚልቁትም ደኅንነቱ የተጠበቀ የጽዳት አገልግሎት የላቸውም ብለዋል። ይህ የአገልግሎት እጥረት በሰዎች የዕድገትና የአህጉሪቱ የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ትልቅ እንቅፋት መሆኑንም አመላክተዋል። ውኃን እንደ ትምህርት፣ ጤና እና ግብርና ትልቅ ትኩረት ሰጥተን ብንሠራበት ኖሮ ይህንን ችግር በቀላሉ መፍታት እንችል ነበር ያሉት ኮሚሽነሩ፤ አሁን ላይ ጉዳዩ ትኩረት በማግኘቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።   በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ዋነኛ ግብ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መሆኑን ተናግረው፤ የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮግራም 45 በመቶ የሚሆነውን የግብርና ምርት በአፍሪካ ለማምረት ግብ ይዞ እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። በተጨማሪ የአፍሪካን የውኃ አካላት ሀብት ወይም ብሉ ኢኮኖሚን ሙሉ በሙሉ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሆነ አንስተው፤ ይህ ዘርፍ ለአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራና ለኢኮኖሚ መነቃቃት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል ነው ያሉት። የአፍሪካን የሰብል ዝርያዎች መጠበቅ መቻል የአህጉሪቱ ኅልውና ጉዳይ መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸው፤ ለዚህም ጠንካራ የዘር ባንኮች ሊኖሩን ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
ሐተታዎች
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 420
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ።   በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 761
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 711
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 929
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 770
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 738
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1337
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3647
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3305
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2149
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7957
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6445
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60064
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54043
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34657
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32218
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27507
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26457
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25989
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25797
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60064
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54043
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34657
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32218
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ዕድሜ  ያልገደበው የልማት አርበኝነት 
Jan 14, 2026 436
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት ብርቱዎች ነገን በማሰብ ሁሌም ታትረው ይሰራሉ፤ ይደክማሉ፤ ይጥራሉ…ለቀጣዩ ትውልድም ጥሪት በማስቀመጥ አሻራቸውን ያኖራሉ። አገር የምትገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው። “አባት ያበጀው፤ ለልጅ ይበጀው” እንደሚባለው ልጆች ከአባቶቻቸው ያገኙትን ጥሪት በአዲስ እውቀትና አሰራር ለአገር እድገት በሚበጅ መልኩ አጠናክረው መጠቀማቸው አይቀርም። “ዕድሜ ጸጋ ነው” የሚለው አባባል አንዳንዴ በዕድሜ ብንገፋም ጠንክረን ከሰራን ብዙ ነገር እናያለን ከሚለው ጋር የተያያዘ ነው። በሰቆጣ ከተማም እድሜ ሳይገድባቸው በልማት ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ለዚህ ማሳያ ናቸው። የከተማዋ ነዋሪ የ67 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ አወቀ እና የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ዕድሜያቸው ቢገፋም ጠንክሮ ከተሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና ዕድሜ ጸጋ ሆኖ ብዙ ለውጥ ማየት እንደሚቻል ማሳያ ናቸው። ግለሰቦቹ ከዕድሜ ብዛት ጉልበቴ ደከመ፣ አይኔ ፈዘዘ፣ እጄም ተሳሰረ…ሳይሉ ጊዜያቸውን በደን፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ በማሳለፍ ለወጣቶች የልማት አርአያነት ያለው ተግባር እየፈጸሙ ነው። አቶ ብርሃኑ አወቀ በሰቆጣ ከተማ ዳርቻ የሚገኝ አለቱ ያገጠጠና የተራቆተ አካባቢን ከሌላ አካባቢ ለም አፈር በማምጣትና በመደልደል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ደን በማልማት ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ነው።   ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከወጣሁ ጀምሮ ጠንክሬ በመስራት የምለወጥበትን ሥራ ማሰብ ስነበረብኝ፤ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ለዘመናት የቆየን ጭንጫ መሬት ጠርጌና ደልድዬ ማልማት ችያለሁ ይላሉ ወደኋላ መልስ ብለው የተነሱበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ። ግማሽ ሄክታር በማይሞላ መሬት ላይ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ዘይቱና፣ ጌሾ፣ ቡና፣ ማንጎና አቮካዶ አልምተዋል። በተጨማሪም ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና ሽንኩርት በማምረት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ጥሪት አፍርተዋል።   ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ተግቶ መስራት ከተቻለ ሀብት ማፍራትና ህይወትንም መለወጥ እንደሚቻል የገለጹት አቶ ብርሀኑ፣ ወጣቱም ከእሳቸው የሥራ ትጋት በመማር በአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ሊጠቀም ይገባል ሲሉ ይመክራሉ። ሌላው የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ባለፉት 18 ዓመታት በተሰማሩበት የአትክልትና ደን ልማት ሥራ የአካባቢያቸውን ገጽታ ቀይረዋል። የዕድሜ ዘመናቸውን በውትድርናና በመንግስት ሠራተኝነት በማገልገል ሃገራዊ ግዳጃቸውን ሲወጡ ነው የቆዩት።   ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከተገለሉ በኋላም ቤት ውስጥ መቀመጥን አልመረጡት። አካፋና ዶማቸውን ይዘው ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ ጌሾ፣ ዘይቱና እና ማንጎ በማልማት ምርቱን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። በአካባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ለይተን ማልማት ከቻልን ድህነትን ማስወገድ የሚከብድ አይሆንም ያሉት አቶ ታደሰ፣ የተራቆተና በጎርፍ የተጎዳን መሬት በማልማት አካባቢውን ሳቢና ማራኪ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት። ወጣቱም ከእሳቸው አርአያነት ያለው ተግባር በመማር በአካባቢው እጁ ላይ ባለ ሀብት ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ማሳየት እንዳለበት መክረዋል።   የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ እንደገለጹት፤ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 24ሺህ 847 አርሶ አደሮች በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል ዕድሜ ሳይገድባቸው ወደ ልማት የገቡ አረጋዊያን እያከናወኑት ያለው የግብርና ልማት ሥራ ለወጣቱ ትልቅ ትምህርት እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከእነሱ ልምድ በመውሰድ በዞኑ ወጣቶች፣ ሴቶችና አረጋዊያን በጓሮና ባላቸው መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህም በዞኑ የሚስተዋለውን የስርዓተ ምግብ ችግር ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
ከማላጋ እስከ አፍሪካ ዋንጫ፤ የሞሮኮው አዲስ እንቁ ብራሂም ዲያዝ
Jan 13, 2026 436
  የግል ክህሎት፣ ፈጣን አስተሳሰቡ እና በጠባብ ክፍተቶች ውስጥ ሰብሮ የመግባት አቅሙ ሙገሳ እንዲጎርፍለት አድርጓል። አንድ ለአንድ ሲገናኝ ተከላካዮችን በፈጣን አካላዊ ቅልጥፍና እና በድንገት አቅጣጫ በመቀየር የሚያልፍበት መንገድ እንዲሁም የመፍጠር አቅሙ የተመልካቾችን ቀልብ የሚይዝ ነው። የአማካይ እና የአጥቂ መስመርን በማገናኘት እና በአስገራሚ ሁኔታ አጭር ኳሶችን በማቀበልም የተዋጣለት ተጫዋች ነው ማለት ይቻላል። በቦታ አያያዙ የእግር ኳስ ልኅቀቱ ከፍተኛ ነው የሚል አድናቆት ከእግር ኳስ ባለሙያዎች አግኝቷል። ኳስን ሲያንከባልልም ለዐይን ይስባል። ከክህሎቱ እና ከማራኪ እንቅስቃሴው ባለፈ ወደ ኋላ እየመለሰ ተከላካዮችን ያግዛል፣ ኳስ ይነጥቃል። ይህ ተጫዋች የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ክስተት የሆነው የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ ነው። የ26 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አምስት ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ነው። አዘጋጇ ሞሮኮ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ኮሞሮስን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የውድድሩን የመጀመሪያ ግብ አስቆጥሯል።   ብራሂም አብዱልቃድር ዲያዝ የተወለደው እ.አ.አ ኦገስት 3 ቀን 1999 በስፔን ማላጋ ግዛት ነው። እናቱ ስፔናዊ አባቱ ሞሮኳዊ ናቸው። ዲያዝ ያደገው በማላጋ ነው። እግር ኳስንም በአንዳሉሺያዊቷ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል። በ16 ዓመቱ ካደገበት ማላጋ በመውጣት እ.አ.አ በ2015 ወደ ማንችስተር ሲቲ ወጣት አካዳሚ በ200 ሺህ ፓውንድ ወጪ ተዘዋወረ። ዲያዝ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2016 በካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ ሊግ ካፕ) ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ባደረገው ጨዋታ በ80ኛው ደቂቃ በኬሌቺ ኢናቺዩ ተቀይሮ በመግባት ለውኃ ሰማያዊዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያውን ጨዋታ ካደረገ ከሶስት ቀናት በኋላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለሶስት ዓመታት የሚያቆየውን ፕሮፌሽናል ኮንትራት ተፈራርሟል። እ.አ.አ ኖቬምበር 21 ቀን 2017 ማንችስተር ሲቲ ከፌይኖርድ ሮተርዳም ጋር ባደረገው የሻምፒዮናስ ሊግ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል። በወቅቱ ብራሂም ስተርሊን መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰዓት ላይ ነበር ተቀይሮ የገባው። ዲያዝ በውኃ ሰማያዊዎቹ ማልያ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የተጫወተው እ.አ.አ ዲሴምበር 19 ቀን 2017 ነው። ማንችስተር ሲቲ ከሌስተር ሲቲ በካራባኦ ካፕ ጨዋታ ላይ ለ88 ደቂቃዎች ተሰልፎ ተጫውቷል።   እ.አ.አ ጃንዋሪ 20 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በወቅቱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ያነሳ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ አራት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ተሳትፎ ያደረገው ብራሂም ዲይዝ የሜዳሊያ ሽልማት አግኝቷል። እ.አ.አ ኦገስት 5 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን 2 ለ 0 ባሸነፈበት የኮሙዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ላይ በፊል ፎደን ተቀይሮ በመግባት ለ15 ደቂቃዎች ተጫውቷል። ዲያዝ እ.አ.አ 2018/19 ማብቂያ ላይ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የመጀመሪያ ግቦቹን ለሲቲ አስቆጥሯል። በማንችስተር ሲቲ ያለው ውል እ.አ.አ 2019 ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት ይነሳ ነበር። ዲያዝ እ.አ.አ ጥር 2019 በ17 ሚሊዮን ዩሮ ከማንችስተር ሲቲ ወደ ሪያል ማድሪድ ተዘዋወረ። ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም ፈርሟል። የክንፍ ተጫዋቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን በነጮቹ ማልያ ያደረገው እ.አ.አ ጥር 9 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ ሌጋኔን በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ 3 ለ 0 ባሸነፈበት ወቅት ነው። ከአራት ቀናት በኋላ በስፔን ላሊጋ ሪያል ማድሪድ ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ ተቀይሮ በመግባት በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያ ግቡን ለማስቆጠር ሶስት ወራትን ጠብቋል። እ.አ.አ ግንቦት 12 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በሪያል ሶሲዬዳድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በወቅቱ ዲያዝ ስድስት ጨዋታዎች ላይ በላሊጋው የተጫወተ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዓመቱ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እ.አ.አ በ2021/21 የውድድር ዓመት ብራሂም ዲያዝ ወደ ኤሲ ሚላን በውሰት ማምራቱን ይፋ አደረገ። ዲያዝ ሚላን እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2020 ክሮቶኔን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ የመጀመሪያ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ ግንቦት 2021 ኤሲ ሚላን ጁቬንቱስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ያስቆጠረው ግብም ተጠቃሽ ነው። ዲያዝ በኤሲ ሚላን የውሰት ውሉ ሲያበቃ በድጋሚ ለሁለት ዓመታት በውሰት የሚቆይበት ስምምነት ሪያል ማድሪድ ከጣልያኑ ክለብ ጋር የተፈራረመ ሲሆን፤ ውሉ ሚላን ተጫዋቹን የማቆየት መብት ሰጥቶታል። እ.አ.አ መስከረም 15 ቀን 2021 ኤሲ ሚላን በሻምፒዮንስ ሊጉ የ3 ለ 2 ሽንፈት ሲያስተናግድ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ግቡን አስቆጥሯል። በ2023 ኤሲ ሚላን ቶተንሃም ሆትስፐርስን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ 1 ለ 0 ሲያሽንፍ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 ሰኔ ወር ላይ ሪያል ማድሪድ ዲያዝ ከኤሲ ሚላን የሶስት ዓመታት የውሰት ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ መመለሱን አሳውቋል። ተጫዋቹ በኤሲ ሚላን ቆይታው 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ዲያዝ ወደ ሪያል ማድሪድ ከተመለሰ በኋላ ኮንትራቱን እስከ 2027 አራዝሟል። እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2023 ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ሪያል ማድሪድ ላስ ፓልማስን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል።   የክንፍ መስመር ተጫዋቹ ሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥ እና በአውሮፓ መድረክ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር እና ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ዲያዝ እስከ አሁን ለሪያል ማድሪድ ባደረጋቸው 129 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከነዚህም ውስጥ 13ቱ በላሊጋው ያስቆጠራቸው ናቸው። ከክለብ ወጣ ስንል የተጫዋቹን የብሔራዊ ቡድን ቆይታ እናገኛለን። ዲያዝ በታዳጊነቱ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ለስፔን ወጣት ቡድኖች ተጫውቷል። እ.አ.አ በ2016/17 የውድድር ዘመን ለስፔን ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ16 ዓመቱ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። በተለይም አዘርባጃን እ.አ.አ በ2017 ባዘጋጀችው 15ኛው የአውሮፓ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ላይ ያሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆት አስችሮታል። በዚያ ቀጥለው በነበሩ ዓመታትም ለስፔን ከ19 እና ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቷል። ብራሂም ዲያዝ በስፔን ታዳጊና ወጣት ቡድኖች ላይ በአጠቃላይ 28 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። የስፔን ታዋቂ የስፖርት ጋዜጣ ማርካ እ.አ.አ ጥር 23 ቀን 2023 ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን መጫወት ማቀዱን የሚመለከት ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ከዜግነቱ ጋር በተያያዘ ያሉ አንዳንድ የአስተደዳር ጉዳዮች በወቅቱ መፍትሄ አግኝተዋል። ይሁንና ኮትዲቯር እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሞሮኮው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከተጫዋቹ ጋር በተደረገ የቅድሚያ ስምምነት ለተጫዋቹ ጥሪ አልተደረገለትም። ዲያዝ እ.አ.አ መጋቢት 10 ቀን 2024 ለሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሀገሪቷ ብሔራዊ መጫወት እንደሚፈልግ በይፋ ማሳወቁን ማርካ በወቅቱ ዘግቧል። ጥያቄውም ተቀባይነት አገኘ። በወቅቱ የሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ብሔራዊ ቡድኑ ከአንጎላ እና ሞሪታኒያ ጋር ለነበረበት የወዳጅነት ጨዋታ ለዲያዝ ጥሪ አድርገውለታል። እ.አ.አ መጋቢት 22 ቀን 2024 ሞሮኮ አንጎላን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። እ.አ.አ ጥቅምት 6 ቀን 2024 ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከጋቦን ጋር ባደረገችው ጨዋታ 4 ለ 1 ስታሸንፍ የመጀመሪያ ግቡን ለሞሮኮ ማስቆጠር ቻለ። እ.አ.አ ሕዳር 15 ቀን 2024 ሞሮኮ በማጣሪያው ጋቦንን 5 ለ 1 ስትረታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። ከሶስት ቀናት በኋላ ሞሮኮ ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ 7 ለ 0 ስታሸንፍ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በሀገሩ ማልያ የመጀመሪያ ሀትሪኩን ሰርቷል። እ.አ.አ ጥቅምት 2025 ሞሮኮ ራባት ላይ ኮንጎ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 በማሸነፍ በስፔን ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተይዞ የነበረውን 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ክብረ ወሰን በመስበር ወደ 16 ማድረስ ችላለች። በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ ላይ ዲያዝ ተሰልፎ ተጫውቷል። የሞሮኮ ተከታታይ የማሸነፍ ጉዞ 19 ጨዋታዎች ደርሶ የነበረ ሲሆን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከማሊ ጋር አንድ አቻ ስትለያይ አብቅቷል።   ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማጣሪያ ብታልፍም አስቀድማ ውድድሩን እንድታዘጋጅ እድል አግኝታ የነበረው ጊኒ በዝግጅት ማነስ ምክንያት በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ከሁለት ዓመት በፊት አዘጋጅነቷ ተነጥቆ ለሞሮኮ ተሰጥቷል። ሞሮኮ የዘንድሮውን ውድድር በደማቅ ሁኔታ እያካሄደች ትገኛለች። በውድድሩ ላይ ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች መካከል ብራሂም ዲያዝ ተጠቃሽ ነው። በአፍሪካ ዋንጫው እስከ አሁን ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። በተሰለፈባቸው በእያንዳዱ ጨዋታዎች ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን በአምስት የአፍሪካ ዋንጫ ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ማሊን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሯል። ሀገሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜ እንድታልፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱንም እየመራ ይገኛል። ሞሮኮ በዚሁ ግስጋሴዋ ከቀጠለች ዲያዝ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና ኮከብ ተጫዋች የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜው ከናይጄሪያ ጋር ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ታደርጋለች። ዲያዝ በዚህ ጨዋታ ላይ ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ የእግር ኳስ ተንታኞች ብራሂም ዲያዝ እ.አ.አ በ2026 ወጥነት ያለው ብቃት ማሳየት ከቻለ የአፍሪካ ኮከብ ተጫዋችነት ሽልማቱን የሚወስድበት የለም እያሉ ይገኛሉ። ሞሮኳውያን በተጫዋቹ ፍቅር ልባቸው ከንፏል። በየጨዋታው ዲያዝ ዲያዝ እያሉ ከፍተኛ ድጋፍ እና ሙገሳ እየሰጡት ይገኛሉ። እሱም በድንቅ ብቃቱ ምላሽ እየሰጣቸው ነው። በተወለደበት ማላጋ ከተማ የጀመረው የእግር ኳስ ሕይወት በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የበለጠ አብቧል። የሞሮኮው አዲሱ ኮከብ ብራሂም ዲያዝ ቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወት በስኬት እና በድል የደመቀ እንደሚሆን ከአሁኑ ድንቅ ብቃቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም