ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ለማምጣት አስችሏል
Oct 18, 2025 36
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ማምጣት ማስቻሉን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ ገለጹ። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ሰባተኛው ሀገር አቀፍ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ዓመታዊ ጉባዔ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባዔው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የፌዴራልና ክልሎች የጤናው ዘርፍ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ናቸው። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ በ2017 በጀት ዓመት የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር የሚያስችል የአዋጅ፣ አሰራር ስርዓት ማሻሻያ ተደርጓል። የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ማምጣት ማስቻሉንም አስረድተዋል። ከመንግስትና አጋር አካላት ጋር የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትን ዲጂታላይዝ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል። ከተቋማት ጋር ውል የተገባለት አቅርቦት ስርዓት በመፈራረም ወደ ስራ መግባቱንም ተናግረዋል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት 68 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ መድኃኒትና ሕክምና ግብዓት መሰራጨቱን ጠቁመው፤ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከ22 ሺህ በላይ የመንግስት ተቋማት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማዘመንና የሀገር ወስጥ አምራቾችን ለማበረታታት የሚያስችል ስራ ተከናውኗል። በዚህም የሀገር ውስጥ አምራቾች ድርሻ 41 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፤ ፈጣንና ተጠያቂነት ያለው ስርዓት ለማጠናከር እንደሚሰራ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከቀይ ባሕርና ከዓባይ ተፋሰስ ጋር የተሰናሰለ ነው
Oct 18, 2025 42
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከቀይ ባሕርና ዓባይ ተፋሰስ ልማት ጋር የተሰናሰለ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ገለጹ። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣በመከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር "የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፥የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ "በሚል ርዕሰ ጉዳይ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ምክክር እየተካሄደ ይገኛል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ፥ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት፣ የስልጡን ህዝቦችና አርበኞች ምድር የሆነችው ኢትዮጵያ ከዓባይ ሸለቆና ከቀይ ባሕር ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያላትና የአፍሪካ ቀንድ አስኳል መሆኗን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከቀይ ባሕርና ከዓባይ ተፋሰስ ልማት ጋር የተሰናሰለ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የጂኦፖለቲካዊ እሳቤም ከሁለቱ የውሃ አካላት ጋር የሚቃኝ መሆኑን በማንሳት፥ ወደ ቀይ ባሕር ስንቀርብ ኃያልነታችንና እሳቤያችን ይሰፋል ብለዋል። ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ያህል ጂኦፖለቲካዊ በሆነው ስለ ቀይ ባሕርም ሆነ ስለባሕር በር ጉዳይ ምርምርና የፖሊሲ ውይይት ማካሄድ ፈጽሞ የማይታሰብ እንደነበር አስታውሰዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮጵያን የቁጭት ዘመን ምላሽ ለመስጠት መንግሥት ስለ ባሕር በር መነጋገር እንደነውር የሚቆጠርበት ዘመን እንዲያከትም ማድረጉን ገልጸዋል። “የሁለቱ ውሃዎች እና የኢትዮጵያ ስትራቴጂያዊ ነፃነት”በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ኮንፈረንስም ሁለቱን ውሃዎች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የእለት ተዕለት አጀንዳ ማድረግ በማስፈለጉ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ከባሕሩ ባሻገር ከራስ ታሪክ፣ጂኦግራፊ፣እውነት፣ ሥነ-ልቦና ጋር መታረቅ ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን ከራስ ጋር የመታረቅ፣ ራስን የመሆንና መፈለግ፣ ከራስ ታሪክና ማንነት ጋር ዕርቅ የመፈጸም ጉዳይ ነው ብለዋል። የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መሀመድ ዑስማን(ዶ/ር)፥ መድረኩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚያስችል ምሁራዊ ውይይት ለማድረግ ወሳኝ ሚና አለው ብለዋል። የኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በርን የማግኘት ፍላጎትም ከታሪክ፣ ጂኦግራፊና ቀጣናዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የሚያያዝ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ኮሞዶር ተገኝ ለታ፥ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብሔራዊ ተጠቃሚነት ከዓባይና ከቀይ ባሕር ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው ብለዋል። ከበርካታ ዓመታት በፊት ፈርሶ የነበረውን የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል መልሶ በማደራጀት በሰው ኃይል፣በአደረጃጀት፣በቴክኖሎጂ አስተማማኝና ጠንካራ ሠራዊት እየተገነባ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በመድረኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፣የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች፣የመከላከያ ሠራዊት መኮንኖችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
የ"መልካ ባሮ"ኢሬቻ በዓል በጋምቤላ ከተማ ተከበረ
Oct 18, 2025 44
ጋምቤላ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦የ"መልካ ባሮ" ኢሬቻ በዓል በጋምቤላ ከተማ የህዝቦችን አብሮነትና ትስስር በሚያጠናክር መልኩ ተከብሯል። "ኢሬቻ ለወንድማማችነትና ለሀገር ማንሰራራት"በሚል መሪ ሀሳብ በጋምቤላ ከተማ በተከበረው በዓል ላይ የተገኙት ታዳሚዎች በዓሉ የህዝብን ማህበራዊ መስተጋብር እንደሚያጠናክር ተናግረዋል። ከበዓሉ ታዳሚዎች መካከል አባገዳ ሀይሉ ለገሰ ለኢዜአ እንደገለፁት፥ ኢሬቻ የኦሮሞ ህዝብ የክረምት መውጣትና የጸደይ ወቅት መግባት ተከትሎ ተሰባስቦ ፈጣሪውን የሚያመሰግንበት በዓል ነው። በዓሉ በአብሮነትና በይቅርታ በአደባባይ የሚከበር ህዝባዊ በዓል መሆኑንም ተናግረዋል። ኢሬቻ የኦሮሞ ህዝብ ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያዊያን በዓል መሆኑን የመልካ ባሮ ኢሬቻ ማሳያ ነው ብለዋል። የጋምቤላ ከተማ የሀገር ሽማግሌ አቶ ኡዶል አጉዋ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፥የኦሮሞ ህዝብ ባህሉንና ወጉን አስጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ ከሚያስችሉት ባህላዊ ሀብቶች መካከል አንዱ የኢሬቻ በዓል። በዓሉ በጋምቤላ ከተማ በድምቀት መከበሩ የኦሮሚያና የጋምቤላ ህዝቦችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑንም ገልፀዋል። የአብሮነትና የወንድማማችነት መገለጫ የሆነው የኢሬቻ በዓል በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መከበሩ የህዝቦችን የእርስ በርስ ትስስርና አንድነትን ያጠናክራል ያሉት ደግሞ ሌላዋ የበዓሉ ታዳሚ ወይዘሮ ቢቂልቱ ቢቂላ ናቸው። ኢሬቻ የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በመቻቻል፣ በመከባበር እና በመፈቃቀር በጋራ የሚኖሩባት ሀገር መሆኗን ከሚያሳዩባቸው ሁነቶች መሆኑንም ተናግረዋል። ዛሬ በጋምቤላ ከተማ በተከበረው የመልካ ባሮ ኢሬቻ በዓል ላይ አባገዳዎች፣ሃደ ሲንቄዎች እንዲሁም የከተማው ነዋሪዎችና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
በኮምቦልቻ ከተማ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ተኪ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ እየተደረገ ነው
Oct 18, 2025 38
ኮምቦልቻ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፡-በኮምቦልቻ ከተማ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ተኪና የውጭ ንግድ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ እየተደረገ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ገለጹ። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በኮምቦልቻ ከተማ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የሥራ እንቅስቃሴ እየጎበኙ ነው። የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድ አሚን የሱፍ በገብኝቱ ላይ እንደገለጹት፤ በከተማው የአምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ተኪና የውጭ ንግድ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ እየተሰራ ነው። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ባለሃብቶች የሚገጥሟቸውን ችግሮች መፍታት መቻሉንም አንስተዋል። በዛሬው ጉብኝት ላይ የሚሰጡ አስተያየቶችን እንደ ግብአት በመጠቀም ከተማዋን ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ተመራጭ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራም ገልጸዋል። በጉብኝቱ ላይ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ እንድሪስ አብዱን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል ሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
በዞኑ ከ42 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ለማልማት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተካሄደ ነው
Oct 18, 2025 41
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፡- በአዊ ብሔረሰብ ዞን በነባርና አዲስ የመስኖ አውታሮች 42ሺህ 123 ሄክታር መሬት ለማልማት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተካሄደ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በበጋው ከሚለማው ከዚሁ መሬት ሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ቤዛዊት ጌታሁን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የመስኖ ልማትን በማስፋፋት በምግብ ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው። በዚህም በዘንድሮ የበጋ ወቅት አርሶ አደሮችን በመደገፍ 42 ሺህ 123 ሄክታር መሬት በነባርና በአዲስ መስኖ ለማልማት ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥ 28ሺህ ሄክታሩ የስንዴ ልማት የሚሸፈን መሆኑን ጠቅሰው፤ ወደ ዘር ስራ ለመግባት አርሶ አደሩን በኩታ ገጠም የማደራጀት፣ የመሬት ልየታና የእርሻ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በስንዴ ከሚለማውም ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቀዋል። ቀሪው መሬት የሚለማው ሽንኩርትን ጨምሮ በተለያየ አትክልት መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ በመስኖ ከሚለማው መሬት ውስጥ ከሁለት ሺህ 500 በላይ ሄክታር በማረስና በማለሳለስ ለዘር ዝግጁ ተደርጓል ብለዋል። የበጋ መስኖ ልማቱን በኩታ ገጠም አሰራርን በመጠቀምና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ ከዚህ ቀደም በሄክታር 37 ኩንታል የነበረው ምርታማነት ወደ 41 ኩንታል ለማሳደግ ግብ መያዙን አንስተዋል። በዞኑ ባለፈው ዓመት ከ20 ሽህ 700 በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ብቻ በማልማት ከ768 ሸህ ኩንታል በላይ ምርት ማግኘት መቻሉን ከግብርና መምሪያው የተገኘ መረጃ ያስረዳል።
ፖለቲካ
በአካባቢያችን ለሚከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን-የምክር ቤት አባላት
Oct 17, 2025 119
ጂንካ፤ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ) :- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመመለስ እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የክትትልና ድጋፍ ስራቸውን እንደሚያጠናክሩ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም በጂንካ ከተማ ተካሄዷል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት በአካባቢያቸው እየተከናወኑ ለሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። የዲላ ሪጂዮ ፖሊሲ ከተማ አስተዳደር ምክትል አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ጂግሶ፤ መንግስት የከተማውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በከተማው የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለስራ ዕድል ፈጠራ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረው የልማት ስራዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድጋፍና ክትትል ተግባራቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚያሸጋግሩ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ዶቦ አዊኖ ናቸው። የደቡብ ኦሞ ዞን ዝናብ አጠር ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ መሆኑን የገለፁት ምክትል አፈ-ጉባኤዋ፤ አርብቶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በመስኖ ልማት እንዲሰማራ መንግስት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ የሚተገበሩ የግብርና ልማት ስራዎች የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የአርብቶ አደሩን ኑሮ እየለወጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአሪ ዞን የገሊላ ከተማ አስተዳደር አማካሪ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ታጋይ ፍላቴ፥ በአካባቢው እምቅ የግብርና አቅም እንዳለ ጠቅሰው በአካባቢው ዓመቱን ሙሉ ማልማት የሚያስችል ምቹ የአየር ጠባይ እና በቂ የውሃ ሀብት አለ ብለዋል። እነዚህን አቀናጅቶ በማልማት የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመለወጥ እየተሰራ ያለው አበረታች ስራ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በአካባቢው ስንዴና ገብስን የመሳሰሉ ሰብሎች በኩታ ገጠም በስፋት እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው፥ ምርቱን ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። በአካባቢው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚያስችሉ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የኮንሶ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ገልገሎ ኦቶማ ናቸው። በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ጠቅሰው፥ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ውጤት ማምጣት መጀመሩን ጠቅሰዋል። በዞኑ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው የህዝቡን አዳጊ ፍላጎት ለማሟላት መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት ከግብ እንዲደርስ ምክር ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው
Oct 17, 2025 117
ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆናቸውን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አመለከተ። የደብረ ብርሃን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13 ዓመት 47ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ መንግስቱ ቤተ እንዳሉት፤ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው። በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፉ ተኪ ምርቶችን በማምረት ገበያን የማረጋጋት ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል። የንግድና ገበያ ማዕከላት ግንባታ ስራዎች ዘመናዊ የግብይት ስርዓት ለመዘርጋት አይነተኛ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል። እነዚህና ሌሎች ተግባራት በበጀት ዓመቱ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም በመንግስት ተቋማት የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ መጓደል ችግሮችን በተደራጀ አግባብ በመፍታት ለህዝቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል። የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ግብርን አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ዕቅድ በጥራትና በተደራሽነት መተግበር እንደሚገባም አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት፤ ባለፉት ወራት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በተከናወኑ የልማትና ሰላምን የማረጋገጥ ተግባራት ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። አሁን ላይም የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ፣ የተቋማትን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የማሳደግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም 269 ለሚሆኑ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከመስጠት ባሻገር 18 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩ በማስፋት ለ1 ሺህ የቤተሰብ መሪዎች ዘመናዊ ቤቶች እንዲገነቡ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። እንዲሁም ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታና መሰል የልማት ተግባራት በትኩረት ይከናወናሉ ሲሉም አብራርተዋል። ምክር ቤቱ ጉባኤውን በነገው ዕለት እንደሚያጠናቅቅ ታውቋል።
ህግ የማስከበር እርምጃው በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል- አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)
Oct 17, 2025 149
ገንዳውሃ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል መንግስት የጀመረው ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በምዕራብ ጎንደር ዞን ከገንዳውሃ፣ መተማ ዮሐንስ ከተማና መተማ ወረዳ ከተውጣጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ሰላም ለማምጣት መንግስት ለሰላማዊ አማራጭ ጭምር እድሎችን በማመቻቸት ብዙ መስራቱን አንስተዋል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበልም በጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን በመፍታት ሰላማዊ ሕይወት እየኖሩ መሆኑን ገልጸው ፤ በዘረፋና እገታ ተግባራቸው የቀጠሉ ጽንፈኞች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን መንግስት ሕግ የማስከበር እርምጃውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል። የመከላከያ ሰራዊት 504ኛ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ሙላው በየነ፤ የመንግስትን የሰላም እድሎች በማይጠቀሙ ፅንፈኞች ላይ ሰራዊቱ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን አረጋግጠዋል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ዘረፋና ግድያ በመፈፀም የሕዝብን ሰላም እያናጋ ያለው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የሚወሰደው ሕግ የማስከበር ተግባር ይቀጥላል ብለዋል። የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሁን መንግሥቱ፤ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት በማስጠበቅ ረገድ ማሕበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ የሕግ ማስከበር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚሕ ረገድ የክልሉ ሕዝብ ከጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ያሳየውን ቀና ትብብር አድንቀው በቀጣይም ድጋፉ እንዳይለይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ፤ የዞኑን ሰላም ለመጠበቅ ከፌዴራልና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሕም በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን አንስተው፤ የሕዝቡ የሰላም ጥረት መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የግጭትና ጦርነት አዙሪት አብቅቶ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል። ከጦርነት ውድመት እንጂ የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን ሁላችንም እንገነዘባለን ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ፤ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የጸጥታ ሃይሉን እናግዛለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ኃላፊነታችንን በብቃት እንወጣለን
Oct 17, 2025 204
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ኃላፊነታቸውን በብቃት እንደሚወጡ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች ቃል በመግባት አረጋገጡ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች "ብሔራዊ ጥቅምና የጂኦስትራቴጂ ቁመና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ውይይት አካሄደዋል። በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ እንዳሉት፤ ጋዜጠኞች ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚያስችሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የበለጠ መስራት አለባቸው። የወል ትርክትን ለመገንባትና የሀገር ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን በመስራት ሙያዊ ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል። ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁ የቀደመውን ትርክት መቀየር ያስቻለ መሆኑን አንስተው፤ የኢትዮጵያን የነገ መስመር የሚቀይሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆናቸውንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ህዝብና ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላት ሃገር ብትሆንም የባህር በር እንደሌላት አንስተው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት በምታደርገው ጥረት ሙያዊ ሀላፊነታቸውን በብቃት መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ተሰሚነትና ተፅዕኖ ፈጣሪነት ለማረጋገጥ የኢዜአ ሰራተኞች ከዜግነት በተጨማሪ ሙያዊ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ነጋሲ አምባዬ የውይይት ጽሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በድህረ እውነት ዘመን የአገር ብልፅግናን ለማረጋገጥ ዘመኑን በሚመጥን ደረጃ ሙያዊ ሃላፊነትን በሚገባ መወጣት ያስፈልጋል። ብሔራዊ ጥቅም የሀገር ህልውና ደህንነት እና ብልፅግና ጉዳይ መሆኑን ጠቁመው፤ የብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና የህዝብና የትውልድ አጀንዳ ለማድረግ የበኩላችንን ሚና ልንወጣ ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ የማንሰራራት ምዕራፍ ላይ ያለች እና ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኗን ያነሱት ደግሞ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተፈራ በቀለ ናቸው። ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ስራዎችን መስራት ከመገናኛ ብዙሃን የሚጠበቅ መሆኑንም ነው የገለፁት። የኢዜአ ሰራተኞች በበኩላቸው በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች እንዲሳኩና የጋራ ትርክትን ለመገንባት የበኩላቸውን ሚና አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሙያዊ ኃላፊነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ ነው
Oct 17, 2025 110
ጭሮ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ አድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ተሰሚነቷን ለማጉላት በዲፕሎማሲው መስክ መንግስት በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል። በዚህ ረገድ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፖለቲካና ዲፕሎማሲው መስክ እንዲሁም ሀገራዊ የምጣኔ ሃብት እድገት እንዲያንሰራራ የሚያደርጉት ጥረት በብዙ መልኩ ይነሳል። ከዙሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ፣ ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን የመገንባት ጅማሮና ኢትዮጵያ የባህር በር እንዲኖራት በመንግስት የተያዘው ጠንካራ አቋም በሁላችንም የሚደገፍ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በዩኒቨርሲቲው የሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ አስተባባሪ የሆኑት ፈቃዱ ወርቁ፤ የመንግስት የዲፕሎማሲና የሀገር ሁለንተናዊ የልማት ጥረት የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የመልማት ፍላጎት እና ብሄራዊ ጥቅም በማንኛውም የውጭ ጫና የማይቀለበስ እንደሆነ የታየበት መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር ተነጥላ ብትቆይም ከዚህ በኋላ ያለ ባህር በር መዝለቅ የማትችል መሆኑን አጽንኦት በመስጠት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስረዳት እየተሄደበት ያለው ርቀት ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል። የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም ለማሟላት በሚያደርገው ጥረት የምሁራን ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ በጥናትና ምርምር እና በተያያዥ ስራዎች ለሀገር ብልጽግና የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከመቸውም ግዜ በበለጠ ባሉት አማራጮች ሁሉ ኢትዮጵያ ላይ የዘመቱት ሀገሪቱ ማንሰራራት በመጀመሯ በመሆኑ ይህንን በመረዳት ሁላችንም ለሀገራችን ብሄራዊ ጥቅም በጋራ መቆም አለብን ብለዋል። ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጋር በሚጻረር መልኩ በግብጽ በኩል የሚሰነዘሩ አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በጠንካራ ዲፕሎማሲ መመከት እንደሚገባም ነው የገለጹት። በቅርቡ አንድ የግብጽ ከፍተኛ ባለስልጣን በሰጡት አስተያየት ላይ የውሀ እና ኢነርጂ ሚንስቴር ያወጣው መግለጫ ትክክለኛና የኢትዮጵያን አቋም በግልጽ ያሳየ መሆኑን በማከል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የህግ ትምህርት ቤት ዲን ዘከርያ አብዱረህማን በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግስት የልማት እቅዶችን ከማሳካት ጎን ለጎን በባህር በር ላይ የያዘው ጽኑ አቋም የሚደገፍ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እየገነባች ባለው ከፍተኛ ኢኮኖሚ እና እየጨመረ ባለው የህዝብ ብዛት የተነሳ የባህር በር አልባ ሆና መቀጠል አትችልም፣ ለዚህም ለመንግስት ቁርጠኛ አቋም ሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ጠንካራ ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በኩል ለሚሰነዘሩ አፍራሽ አጀንዳዎች መንግስት በዲፕሎማሲያዊ ጥብበ መመከቱን መቀጠል እንዳለበትም አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ እና በዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ ነው
Oct 17, 2025 136
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እና ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑን የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ገልጸዋል። የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የኅልውና ጉዳይ መሆኑንም ነው በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህሩ ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ለኢዜአ የተናገሩት። ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑንም በአጽንኦት አንስተዋል። እስካሁን ባለው ሂደትም በብዙ መመዘኛዎች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እንዳለው መገንዘባቸውን ገልጸዋል። ለውጤታማነቱም ኢትዮጵያ ያላትን ሕጋዊ መሠረት፣ ታሪካዊና የሠነድ ማስረጃ በመጠቀም በሰላማዊ የዲፕሎማሲ ልዕልና ስልት ጥረቷን በይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅባትም መክረዋል። ለዚህም አጋዡ መሣሪያ ለጎረቤት ሀገራት፣ ለአፍሪካ ኅብረት፣ ለምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለሥልጣን(ኢጋድ)፣ ለዓለም አቀፍ ተቋማትና ተጽዕኖ ፈጣሪ የጋራ ዕድገት ደጋፊ ሀገራት የአቋሟን ትክክለኛነት በልኩ ማስገንዘብ መሆኑን አስረድተዋል። የባሕር በር ለተሻለ ሁለንተናዊ ዕድገት ቁልፍ መሆኑን አስገንዝበው፤ ከሕግና ከሕዝብ ፍላጎት ውጭ በሆነ መንገድ እንድታጣ የተደረገችውን የባህር በር ማግኘት እንደሚገባትም ነው የተናገሩት።
የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት በሰላምና ፀጥታ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Oct 17, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት በሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ያላቸውን የጋራ አጋርነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አባላትን ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተቀብለው አነጋግረዋል። ሊቀመንበሩ የምክር ቤቱ አባላትን ሰላም፣ ደህንነት እና ልማትን ጨምሮ የአፍሪካ ህብረት ቁልፍ የትኩረት መስኮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። ዩሱፍ የአፍሪካ ህብረት እና የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አጋርነት አፍሪካን በመወከል በተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆነው እያገለገሉ ያሉ ሀገራት ማዕቀፍ (A3) አማካኝነት ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። አፍሪካ በምክር ቤቱ ቋሚ ውክልና ማግኘት እንዳለባት አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ መር የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎችን አስመልክቶ ያፀደቀውን የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 2719 በማንሳት የሰላም ማስከበር ስራው ለአፍሪካ ዘላቂ መረጋጋት እጅጉን ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት የአፍሪካ ህብረትን አመራር ሰጪነት አድንቀዋል። አባላቱ የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ሰላም፣ ደህንነት እና ዘላቂ ልማትን ጨምሮ የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ የአፍሪካ አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በአዲስ አበባ የጋራ ምክክራቸውን ዛሬ ማድረግ የጀመሩ ሲሆን ውይይቱ እስከ ነገ ይቆያል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ለጀመሩት ፕሮጀክት ድጋፍ ላደረጉ ለጋሾች የእራት ግብዣ አደረጉ
Oct 16, 2025 213
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጀመሩት የአዳራሽ እና አካባቢን የማስዋብ ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ ለጋሾችችና ባለሀብቶች የእራት ግብዣ አድርገዋል። ፕሬዝደንቱ በነጩ ቤተ መንግስት የእራት ግብዣውን ያደረጉት አዲሱን የኋይት ሀውስ ታላቅ አዳራሽ እና አካባቢን የማስዋብ የ200 ሚሊየን ዶላር ፕሮጀክት ለሚደግፉ ለጋሾች እና ባለሃብቶች መሆኑም ተገልጿል። ግንባታው ባለፈው መስከረም ወር የተጀመረውና 90 ሺህ ስኩዌር ጫማ(8 ሺህ 361 ካሬ ሜትር) አዳራሽ በ10 ሺዎች የሚቀጠሩ እንግዶችን ያስተናግዳልም ተብሏል። በዚህ ወቅት ፕሬዝዳንቱ አንደገለጹት ፕሮጀክቱ አሜሪካን በዓለም መድረክ በተሻለ ሁኔታ እንዲወክል የሚያስችል ነው። አሁን ላይ ያለው መሠረተ ልማት መሪዎችን ለመቀበል እና ለማነጋገር ብሎም የተለያዩ ሁነቶችን ለማስተናገድ ምቹ አለመሆኑንም አንስተዋል። የታላቁ አዳራሽ ፕሮጀክት ከኋይት ሀውስ ንድፍ ጋር የሚስማማ ተደርጎ እንደሚገነባ ገልጸው፤ ለፕሮጀክቱ ድጋፍ እያደረጉ የሚገኙ ባለሃብቶች እና ኩባንያዎችንም አመስግነዋል። የአሜሪካው የመከላከያና አይሮስፔስ ካምፓኔ ፣የማይክሮሶፍት፣ የሜታ፣ የጉግል፣ የአማዞን እና የቲ-ሞባይል ተወካዮችን ጨምሮ በርካታ የክሪፕቶ ስራ ፈጣሪዎች እና ባለሃብቶች መገኘታቸውን ሲኤን ኤን ዘግቦታል። ዛሬ ላይ ፕሬዝዳንቱ የጀመሩት ‘የሌጋሲ ዲነር’ ስራ ቀደም ባሉት ዓመታት በአዲስ አበባ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት በሚል መጀመሩ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለፕሮጀክቶቹ ትግበራ ገንዘቡን በ“ገበታ ለሸገር” የእራት ምሽት ፕሮግራም በማዘጋጀት ሀገር ወዳድ ባለሀብቶችም በአምስት ሚሊዮን ብር ገበታውን በመቋደስ አሻራቸውን አኑረዋል። ይህ እንቅስቃሴም አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ ከማድረግ ጀምሮ ዜጎች እና ባለሀብቶች የነቃ ተሳትፎ ባደረጉበት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ከአዲስ አበባ ውጪም ማለትም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮይሻ፣ በአማራ ክልል ጎርጎራ፣ በኦሮሚያ ክልል ደግሞ ወንጪን ማልማት ተችሏል።
ፖለቲካ
በአካባቢያችን ለሚከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን-የምክር ቤት አባላት
Oct 17, 2025 119
ጂንካ፤ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ) :- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመመለስ እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የክትትልና ድጋፍ ስራቸውን እንደሚያጠናክሩ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም በጂንካ ከተማ ተካሄዷል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት በአካባቢያቸው እየተከናወኑ ለሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። የዲላ ሪጂዮ ፖሊሲ ከተማ አስተዳደር ምክትል አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ጂግሶ፤ መንግስት የከተማውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በከተማው የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለስራ ዕድል ፈጠራ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረው የልማት ስራዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድጋፍና ክትትል ተግባራቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚያሸጋግሩ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ዶቦ አዊኖ ናቸው። የደቡብ ኦሞ ዞን ዝናብ አጠር ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ መሆኑን የገለፁት ምክትል አፈ-ጉባኤዋ፤ አርብቶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በመስኖ ልማት እንዲሰማራ መንግስት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ የሚተገበሩ የግብርና ልማት ስራዎች የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የአርብቶ አደሩን ኑሮ እየለወጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአሪ ዞን የገሊላ ከተማ አስተዳደር አማካሪ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ታጋይ ፍላቴ፥ በአካባቢው እምቅ የግብርና አቅም እንዳለ ጠቅሰው በአካባቢው ዓመቱን ሙሉ ማልማት የሚያስችል ምቹ የአየር ጠባይ እና በቂ የውሃ ሀብት አለ ብለዋል። እነዚህን አቀናጅቶ በማልማት የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመለወጥ እየተሰራ ያለው አበረታች ስራ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በአካባቢው ስንዴና ገብስን የመሳሰሉ ሰብሎች በኩታ ገጠም በስፋት እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው፥ ምርቱን ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። በአካባቢው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚያስችሉ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የኮንሶ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ገልገሎ ኦቶማ ናቸው። በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ጠቅሰው፥ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ውጤት ማምጣት መጀመሩን ጠቅሰዋል። በዞኑ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው የህዝቡን አዳጊ ፍላጎት ለማሟላት መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት ከግብ እንዲደርስ ምክር ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው
Oct 17, 2025 117
ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆናቸውን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አመለከተ። የደብረ ብርሃን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13 ዓመት 47ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ መንግስቱ ቤተ እንዳሉት፤ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው። በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፉ ተኪ ምርቶችን በማምረት ገበያን የማረጋጋት ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል። የንግድና ገበያ ማዕከላት ግንባታ ስራዎች ዘመናዊ የግብይት ስርዓት ለመዘርጋት አይነተኛ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል። እነዚህና ሌሎች ተግባራት በበጀት ዓመቱ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም በመንግስት ተቋማት የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ መጓደል ችግሮችን በተደራጀ አግባብ በመፍታት ለህዝቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል። የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ግብርን አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ዕቅድ በጥራትና በተደራሽነት መተግበር እንደሚገባም አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት፤ ባለፉት ወራት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በተከናወኑ የልማትና ሰላምን የማረጋገጥ ተግባራት ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። አሁን ላይም የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ፣ የተቋማትን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የማሳደግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም 269 ለሚሆኑ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከመስጠት ባሻገር 18 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩ በማስፋት ለ1 ሺህ የቤተሰብ መሪዎች ዘመናዊ ቤቶች እንዲገነቡ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። እንዲሁም ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታና መሰል የልማት ተግባራት በትኩረት ይከናወናሉ ሲሉም አብራርተዋል። ምክር ቤቱ ጉባኤውን በነገው ዕለት እንደሚያጠናቅቅ ታውቋል።
ህግ የማስከበር እርምጃው በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል- አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)
Oct 17, 2025 149
ገንዳውሃ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል መንግስት የጀመረው ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በምዕራብ ጎንደር ዞን ከገንዳውሃ፣ መተማ ዮሐንስ ከተማና መተማ ወረዳ ከተውጣጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ሰላም ለማምጣት መንግስት ለሰላማዊ አማራጭ ጭምር እድሎችን በማመቻቸት ብዙ መስራቱን አንስተዋል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበልም በጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን በመፍታት ሰላማዊ ሕይወት እየኖሩ መሆኑን ገልጸው ፤ በዘረፋና እገታ ተግባራቸው የቀጠሉ ጽንፈኞች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን መንግስት ሕግ የማስከበር እርምጃውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል። የመከላከያ ሰራዊት 504ኛ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ሙላው በየነ፤ የመንግስትን የሰላም እድሎች በማይጠቀሙ ፅንፈኞች ላይ ሰራዊቱ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን አረጋግጠዋል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ዘረፋና ግድያ በመፈፀም የሕዝብን ሰላም እያናጋ ያለው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የሚወሰደው ሕግ የማስከበር ተግባር ይቀጥላል ብለዋል። የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሁን መንግሥቱ፤ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት በማስጠበቅ ረገድ ማሕበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ የሕግ ማስከበር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚሕ ረገድ የክልሉ ሕዝብ ከጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ያሳየውን ቀና ትብብር አድንቀው በቀጣይም ድጋፉ እንዳይለይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ፤ የዞኑን ሰላም ለመጠበቅ ከፌዴራልና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሕም በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን አንስተው፤ የሕዝቡ የሰላም ጥረት መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የግጭትና ጦርነት አዙሪት አብቅቶ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል። ከጦርነት ውድመት እንጂ የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን ሁላችንም እንገነዘባለን ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ፤ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የጸጥታ ሃይሉን እናግዛለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ኃላፊነታችንን በብቃት እንወጣለን
Oct 17, 2025 204
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ኃላፊነታቸውን በብቃት እንደሚወጡ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች ቃል በመግባት አረጋገጡ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች "ብሔራዊ ጥቅምና የጂኦስትራቴጂ ቁመና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ውይይት አካሄደዋል። በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ እንዳሉት፤ ጋዜጠኞች ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚያስችሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የበለጠ መስራት አለባቸው። የወል ትርክትን ለመገንባትና የሀገር ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን በመስራት ሙያዊ ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል። ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁ የቀደመውን ትርክት መቀየር ያስቻለ መሆኑን አንስተው፤ የኢትዮጵያን የነገ መስመር የሚቀይሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆናቸውንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ህዝብና ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላት ሃገር ብትሆንም የባህር በር እንደሌላት አንስተው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት በምታደርገው ጥረት ሙያዊ ሀላፊነታቸውን በብቃት መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ተሰሚነትና ተፅዕኖ ፈጣሪነት ለማረጋገጥ የኢዜአ ሰራተኞች ከዜግነት በተጨማሪ ሙያዊ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ነጋሲ አምባዬ የውይይት ጽሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በድህረ እውነት ዘመን የአገር ብልፅግናን ለማረጋገጥ ዘመኑን በሚመጥን ደረጃ ሙያዊ ሃላፊነትን በሚገባ መወጣት ያስፈልጋል። ብሔራዊ ጥቅም የሀገር ህልውና ደህንነት እና ብልፅግና ጉዳይ መሆኑን ጠቁመው፤ የብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና የህዝብና የትውልድ አጀንዳ ለማድረግ የበኩላችንን ሚና ልንወጣ ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ የማንሰራራት ምዕራፍ ላይ ያለች እና ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኗን ያነሱት ደግሞ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተፈራ በቀለ ናቸው። ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ስራዎችን መስራት ከመገናኛ ብዙሃን የሚጠበቅ መሆኑንም ነው የገለፁት። የኢዜአ ሰራተኞች በበኩላቸው በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች እንዲሳኩና የጋራ ትርክትን ለመገንባት የበኩላቸውን ሚና አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሙያዊ ኃላፊነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ ነው
Oct 17, 2025 110
ጭሮ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ አድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ተሰሚነቷን ለማጉላት በዲፕሎማሲው መስክ መንግስት በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል። በዚህ ረገድ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፖለቲካና ዲፕሎማሲው መስክ እንዲሁም ሀገራዊ የምጣኔ ሃብት እድገት እንዲያንሰራራ የሚያደርጉት ጥረት በብዙ መልኩ ይነሳል። ከዙሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ፣ ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን የመገንባት ጅማሮና ኢትዮጵያ የባህር በር እንዲኖራት በመንግስት የተያዘው ጠንካራ አቋም በሁላችንም የሚደገፍ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በዩኒቨርሲቲው የሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ አስተባባሪ የሆኑት ፈቃዱ ወርቁ፤ የመንግስት የዲፕሎማሲና የሀገር ሁለንተናዊ የልማት ጥረት የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የመልማት ፍላጎት እና ብሄራዊ ጥቅም በማንኛውም የውጭ ጫና የማይቀለበስ እንደሆነ የታየበት መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር ተነጥላ ብትቆይም ከዚህ በኋላ ያለ ባህር በር መዝለቅ የማትችል መሆኑን አጽንኦት በመስጠት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስረዳት እየተሄደበት ያለው ርቀት ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል። የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም ለማሟላት በሚያደርገው ጥረት የምሁራን ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ በጥናትና ምርምር እና በተያያዥ ስራዎች ለሀገር ብልጽግና የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከመቸውም ግዜ በበለጠ ባሉት አማራጮች ሁሉ ኢትዮጵያ ላይ የዘመቱት ሀገሪቱ ማንሰራራት በመጀመሯ በመሆኑ ይህንን በመረዳት ሁላችንም ለሀገራችን ብሄራዊ ጥቅም በጋራ መቆም አለብን ብለዋል። ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጋር በሚጻረር መልኩ በግብጽ በኩል የሚሰነዘሩ አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በጠንካራ ዲፕሎማሲ መመከት እንደሚገባም ነው የገለጹት። በቅርቡ አንድ የግብጽ ከፍተኛ ባለስልጣን በሰጡት አስተያየት ላይ የውሀ እና ኢነርጂ ሚንስቴር ያወጣው መግለጫ ትክክለኛና የኢትዮጵያን አቋም በግልጽ ያሳየ መሆኑን በማከል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የህግ ትምህርት ቤት ዲን ዘከርያ አብዱረህማን በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግስት የልማት እቅዶችን ከማሳካት ጎን ለጎን በባህር በር ላይ የያዘው ጽኑ አቋም የሚደገፍ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እየገነባች ባለው ከፍተኛ ኢኮኖሚ እና እየጨመረ ባለው የህዝብ ብዛት የተነሳ የባህር በር አልባ ሆና መቀጠል አትችልም፣ ለዚህም ለመንግስት ቁርጠኛ አቋም ሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ጠንካራ ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በኩል ለሚሰነዘሩ አፍራሽ አጀንዳዎች መንግስት በዲፕሎማሲያዊ ጥብበ መመከቱን መቀጠል እንዳለበትም አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ እና በዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ ነው
Oct 17, 2025 136
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እና ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑን የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ገልጸዋል። የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የኅልውና ጉዳይ መሆኑንም ነው በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህሩ ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ለኢዜአ የተናገሩት። ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑንም በአጽንኦት አንስተዋል። እስካሁን ባለው ሂደትም በብዙ መመዘኛዎች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እንዳለው መገንዘባቸውን ገልጸዋል። ለውጤታማነቱም ኢትዮጵያ ያላትን ሕጋዊ መሠረት፣ ታሪካዊና የሠነድ ማስረጃ በመጠቀም በሰላማዊ የዲፕሎማሲ ልዕልና ስልት ጥረቷን በይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅባትም መክረዋል። ለዚህም አጋዡ መሣሪያ ለጎረቤት ሀገራት፣ ለአፍሪካ ኅብረት፣ ለምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለሥልጣን(ኢጋድ)፣ ለዓለም አቀፍ ተቋማትና ተጽዕኖ ፈጣሪ የጋራ ዕድገት ደጋፊ ሀገራት የአቋሟን ትክክለኛነት በልኩ ማስገንዘብ መሆኑን አስረድተዋል። የባሕር በር ለተሻለ ሁለንተናዊ ዕድገት ቁልፍ መሆኑን አስገንዝበው፤ ከሕግና ከሕዝብ ፍላጎት ውጭ በሆነ መንገድ እንድታጣ የተደረገችውን የባህር በር ማግኘት እንደሚገባትም ነው የተናገሩት።
የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት በሰላምና ፀጥታ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Oct 17, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት በሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ያላቸውን የጋራ አጋርነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አባላትን ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተቀብለው አነጋግረዋል። ሊቀመንበሩ የምክር ቤቱ አባላትን ሰላም፣ ደህንነት እና ልማትን ጨምሮ የአፍሪካ ህብረት ቁልፍ የትኩረት መስኮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። ዩሱፍ የአፍሪካ ህብረት እና የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አጋርነት አፍሪካን በመወከል በተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆነው እያገለገሉ ያሉ ሀገራት ማዕቀፍ (A3) አማካኝነት ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። አፍሪካ በምክር ቤቱ ቋሚ ውክልና ማግኘት እንዳለባት አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ መር የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎችን አስመልክቶ ያፀደቀውን የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 2719 በማንሳት የሰላም ማስከበር ስራው ለአፍሪካ ዘላቂ መረጋጋት እጅጉን ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት የአፍሪካ ህብረትን አመራር ሰጪነት አድንቀዋል። አባላቱ የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ሰላም፣ ደህንነት እና ዘላቂ ልማትን ጨምሮ የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ የአፍሪካ አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በአዲስ አበባ የጋራ ምክክራቸውን ዛሬ ማድረግ የጀመሩ ሲሆን ውይይቱ እስከ ነገ ይቆያል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ለጀመሩት ፕሮጀክት ድጋፍ ላደረጉ ለጋሾች የእራት ግብዣ አደረጉ
Oct 16, 2025 213
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጀመሩት የአዳራሽ እና አካባቢን የማስዋብ ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ ለጋሾችችና ባለሀብቶች የእራት ግብዣ አድርገዋል። ፕሬዝደንቱ በነጩ ቤተ መንግስት የእራት ግብዣውን ያደረጉት አዲሱን የኋይት ሀውስ ታላቅ አዳራሽ እና አካባቢን የማስዋብ የ200 ሚሊየን ዶላር ፕሮጀክት ለሚደግፉ ለጋሾች እና ባለሃብቶች መሆኑም ተገልጿል። ግንባታው ባለፈው መስከረም ወር የተጀመረውና 90 ሺህ ስኩዌር ጫማ(8 ሺህ 361 ካሬ ሜትር) አዳራሽ በ10 ሺዎች የሚቀጠሩ እንግዶችን ያስተናግዳልም ተብሏል። በዚህ ወቅት ፕሬዝዳንቱ አንደገለጹት ፕሮጀክቱ አሜሪካን በዓለም መድረክ በተሻለ ሁኔታ እንዲወክል የሚያስችል ነው። አሁን ላይ ያለው መሠረተ ልማት መሪዎችን ለመቀበል እና ለማነጋገር ብሎም የተለያዩ ሁነቶችን ለማስተናገድ ምቹ አለመሆኑንም አንስተዋል። የታላቁ አዳራሽ ፕሮጀክት ከኋይት ሀውስ ንድፍ ጋር የሚስማማ ተደርጎ እንደሚገነባ ገልጸው፤ ለፕሮጀክቱ ድጋፍ እያደረጉ የሚገኙ ባለሃብቶች እና ኩባንያዎችንም አመስግነዋል። የአሜሪካው የመከላከያና አይሮስፔስ ካምፓኔ ፣የማይክሮሶፍት፣ የሜታ፣ የጉግል፣ የአማዞን እና የቲ-ሞባይል ተወካዮችን ጨምሮ በርካታ የክሪፕቶ ስራ ፈጣሪዎች እና ባለሃብቶች መገኘታቸውን ሲኤን ኤን ዘግቦታል። ዛሬ ላይ ፕሬዝዳንቱ የጀመሩት ‘የሌጋሲ ዲነር’ ስራ ቀደም ባሉት ዓመታት በአዲስ አበባ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት በሚል መጀመሩ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለፕሮጀክቶቹ ትግበራ ገንዘቡን በ“ገበታ ለሸገር” የእራት ምሽት ፕሮግራም በማዘጋጀት ሀገር ወዳድ ባለሀብቶችም በአምስት ሚሊዮን ብር ገበታውን በመቋደስ አሻራቸውን አኑረዋል። ይህ እንቅስቃሴም አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ ከማድረግ ጀምሮ ዜጎች እና ባለሀብቶች የነቃ ተሳትፎ ባደረጉበት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ከአዲስ አበባ ውጪም ማለትም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮይሻ፣ በአማራ ክልል ጎርጎራ፣ በኦሮሚያ ክልል ደግሞ ወንጪን ማልማት ተችሏል።
ማህበራዊ
የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ለማምጣት አስችሏል
Oct 18, 2025 36
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ማምጣት ማስቻሉን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ ገለጹ። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ሰባተኛው ሀገር አቀፍ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ዓመታዊ ጉባዔ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባዔው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የፌዴራልና ክልሎች የጤናው ዘርፍ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ናቸው። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ በ2017 በጀት ዓመት የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር የሚያስችል የአዋጅ፣ አሰራር ስርዓት ማሻሻያ ተደርጓል። የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ማምጣት ማስቻሉንም አስረድተዋል። ከመንግስትና አጋር አካላት ጋር የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትን ዲጂታላይዝ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል። ከተቋማት ጋር ውል የተገባለት አቅርቦት ስርዓት በመፈራረም ወደ ስራ መግባቱንም ተናግረዋል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት 68 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ መድኃኒትና ሕክምና ግብዓት መሰራጨቱን ጠቁመው፤ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከ22 ሺህ በላይ የመንግስት ተቋማት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማዘመንና የሀገር ወስጥ አምራቾችን ለማበረታታት የሚያስችል ስራ ተከናውኗል። በዚህም የሀገር ውስጥ አምራቾች ድርሻ 41 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፤ ፈጣንና ተጠያቂነት ያለው ስርዓት ለማጠናከር እንደሚሰራ ተናግረዋል።
የ"መልካ ባሮ"ኢሬቻ በዓል በጋምቤላ ከተማ ተከበረ
Oct 18, 2025 44
ጋምቤላ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦የ"መልካ ባሮ" ኢሬቻ በዓል በጋምቤላ ከተማ የህዝቦችን አብሮነትና ትስስር በሚያጠናክር መልኩ ተከብሯል። "ኢሬቻ ለወንድማማችነትና ለሀገር ማንሰራራት"በሚል መሪ ሀሳብ በጋምቤላ ከተማ በተከበረው በዓል ላይ የተገኙት ታዳሚዎች በዓሉ የህዝብን ማህበራዊ መስተጋብር እንደሚያጠናክር ተናግረዋል። ከበዓሉ ታዳሚዎች መካከል አባገዳ ሀይሉ ለገሰ ለኢዜአ እንደገለፁት፥ ኢሬቻ የኦሮሞ ህዝብ የክረምት መውጣትና የጸደይ ወቅት መግባት ተከትሎ ተሰባስቦ ፈጣሪውን የሚያመሰግንበት በዓል ነው። በዓሉ በአብሮነትና በይቅርታ በአደባባይ የሚከበር ህዝባዊ በዓል መሆኑንም ተናግረዋል። ኢሬቻ የኦሮሞ ህዝብ ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያዊያን በዓል መሆኑን የመልካ ባሮ ኢሬቻ ማሳያ ነው ብለዋል። የጋምቤላ ከተማ የሀገር ሽማግሌ አቶ ኡዶል አጉዋ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፥የኦሮሞ ህዝብ ባህሉንና ወጉን አስጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ ከሚያስችሉት ባህላዊ ሀብቶች መካከል አንዱ የኢሬቻ በዓል። በዓሉ በጋምቤላ ከተማ በድምቀት መከበሩ የኦሮሚያና የጋምቤላ ህዝቦችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑንም ገልፀዋል። የአብሮነትና የወንድማማችነት መገለጫ የሆነው የኢሬቻ በዓል በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መከበሩ የህዝቦችን የእርስ በርስ ትስስርና አንድነትን ያጠናክራል ያሉት ደግሞ ሌላዋ የበዓሉ ታዳሚ ወይዘሮ ቢቂልቱ ቢቂላ ናቸው። ኢሬቻ የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በመቻቻል፣ በመከባበር እና በመፈቃቀር በጋራ የሚኖሩባት ሀገር መሆኗን ከሚያሳዩባቸው ሁነቶች መሆኑንም ተናግረዋል። ዛሬ በጋምቤላ ከተማ በተከበረው የመልካ ባሮ ኢሬቻ በዓል ላይ አባገዳዎች፣ሃደ ሲንቄዎች እንዲሁም የከተማው ነዋሪዎችና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
በጤናው ዘርፍ የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የአጋር ድርጅቶች ትብብርና እገዛ የላቀ ትርጉም አለው
Oct 17, 2025 117
ሀዋሳ ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፦ በጤናው ዘርፍ የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የአጋር ድርጅቶች ትብብርና እገዛ የላቀ ትርጉም ያለው መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እና የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ሜሪጆይ ኢትዮጵያ በሀዋሳ ያቋቋመውን የኩላሊት እጥበት ማዕከል መርቀው በይፋ ስራ አስጀምረዋል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ የጤና ዘርፍ አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ተግባራት የአጋር ድርጅቶች እገዛ ትልቅ ትርጉም አለው። በመሆኑም ሜሪጆይ ኢትዮጵያ በሀዋሳ የጀመረው የሆስፒታል ግንባታና ዛሬ ያስመረቀው የኩላሊት እጥበት ማዕከል የክልሉ መንግስት በሚያከናውነው የጤና ልማት ስራ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል። የክልሉ መንግስት የማዕከሉ አገልግሎት ዘላቂነት እንዲኖረው አስፈላጊውን እገዛ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠው በዛሬው እለት የ10 ሚሊዮን ብር እና የአምቡላንስ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው የኩላሊት በሽታን ለመከላከል በጥናት ላይ የተመሰረተ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ለበሽታው ታማሚዎችም የህክምና ጥራትና አገልግሎት ተደራሽነትን ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል። በመሆኑም ሜሪጆይ ኢትዮጵያ በሀዋሳ ያቋቋመው የኩላሊት እጥበት ማዕከል መንግስት የጤናውን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጀመራቸውን ስራዎች የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የማዕከሉ አገልግሎት የተሟላና ዘላቂነት ያለው እንዲሆን ጤና ሚኒስቴርና የክልሉ ጤና ቢሮ አስፈላጊውን እገዛና ድጋፍ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል። ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በ29 ሚሊዮን ብር ያቋቋመውን የኩላሊት እጥበት ማዕከል ድጋፍ ለሚያደርግላቸው አረጋውያን እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ህሙማን ቅድሚያ በመስጠት አገልግሎት እንደሚሰጥ የገለጹት ደግሞ የሜሪጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ስራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ናቸው፡፡ ማእከሉ ከሌሎች ህክምና ማዕከላት ባነሰ ክፍያ ከሰኞ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ገልፀው ህብረተሰቡ የማዕከሉ አባል በመሆን የአገልግሎቱን ቀጣይነት እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል፡፡ የኩላሊት እጥበት ከጀመሩ አምስት ዓመት እንደሆናቸው የተናገሩት የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው አቶ ታገሰ ፋንቱ በበኩላቸው የማእከሉ መከፈት ኢኮኖሚያዊ ጫናቸውን እንደሚያቃልልላቸው ተናግረዋል፡፡ በማዕከሉ መከፈት መደሰታቸውን ገልጸው አገልግሎቱን ለማግኘትም የአባልነት ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተክሌ ጆምባም ለማዕከሉ የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ባለሃብቶችና የተለያዩ ተቋማት፣ እንዲሁም ግለሰቦች የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
ለትምህርት የደረሱ ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ ብቁ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት የወላጆች ሚና እና ሃላፊነት ከፍተኛ ነው
Oct 17, 2025 93
ጋምቤላ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፦ ለትምህርት የደረሱ ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ ብቁ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት የወላጆች ሚና እና ሃላፊነት ከፍተኛ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በጋምቤላ ክልል አዳሪ ትምህርት ቤት እና ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ በዛሬው እለት አስጀምረዋል። ሚኒስትሩ መርሃ ግብሩን ተከትሎ በጋምቤላ ከተማ በራስ ጉበና 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወላጆች እና የትምህርት ማህበረሰብ አካላት የውይይት መድረክ ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል። ሚኒስትሩ በመልክታቸውም ሀገር ተረካቢው ትውልድ የተሻለ እንዲሆንና ለሀገሩ ውጤታማ ስራ እንዲሰራ በትምህርት ሂደት ውስጥ ማለፍ ይጠበቅበታል ብለዋል። በተለይም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናትን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ ቤተሰባዊ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን ግዴታ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ለትምህርት የደረሱ ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ ብቁ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት የወላጆች ሚና እና ሃላፊነት ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። ትውልዱ በክህሎትና በስነ- ምግባር ታንፆ ካለደገ ነገ ሀገር በመረከብ ረገድ ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል የገለጹት ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ ወላጆችና የትምህርት ማህበረሰቡ ትልቅ ሃላፊነት አለባቸው ብለዋል። መንግስት ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናትን የትምህርት እድል ተጠቃሚ በማድረግ የትውልድ ግንባታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸው አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከቀይ ባሕርና ከዓባይ ተፋሰስ ጋር የተሰናሰለ ነው
Oct 18, 2025 42
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከቀይ ባሕርና ዓባይ ተፋሰስ ልማት ጋር የተሰናሰለ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ገለጹ። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣በመከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር "የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፥የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ "በሚል ርዕሰ ጉዳይ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ምክክር እየተካሄደ ይገኛል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ፥ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት፣ የስልጡን ህዝቦችና አርበኞች ምድር የሆነችው ኢትዮጵያ ከዓባይ ሸለቆና ከቀይ ባሕር ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያላትና የአፍሪካ ቀንድ አስኳል መሆኗን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከቀይ ባሕርና ከዓባይ ተፋሰስ ልማት ጋር የተሰናሰለ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የጂኦፖለቲካዊ እሳቤም ከሁለቱ የውሃ አካላት ጋር የሚቃኝ መሆኑን በማንሳት፥ ወደ ቀይ ባሕር ስንቀርብ ኃያልነታችንና እሳቤያችን ይሰፋል ብለዋል። ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ያህል ጂኦፖለቲካዊ በሆነው ስለ ቀይ ባሕርም ሆነ ስለባሕር በር ጉዳይ ምርምርና የፖሊሲ ውይይት ማካሄድ ፈጽሞ የማይታሰብ እንደነበር አስታውሰዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮጵያን የቁጭት ዘመን ምላሽ ለመስጠት መንግሥት ስለ ባሕር በር መነጋገር እንደነውር የሚቆጠርበት ዘመን እንዲያከትም ማድረጉን ገልጸዋል። “የሁለቱ ውሃዎች እና የኢትዮጵያ ስትራቴጂያዊ ነፃነት”በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ኮንፈረንስም ሁለቱን ውሃዎች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የእለት ተዕለት አጀንዳ ማድረግ በማስፈለጉ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ከባሕሩ ባሻገር ከራስ ታሪክ፣ጂኦግራፊ፣እውነት፣ ሥነ-ልቦና ጋር መታረቅ ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን ከራስ ጋር የመታረቅ፣ ራስን የመሆንና መፈለግ፣ ከራስ ታሪክና ማንነት ጋር ዕርቅ የመፈጸም ጉዳይ ነው ብለዋል። የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መሀመድ ዑስማን(ዶ/ር)፥ መድረኩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚያስችል ምሁራዊ ውይይት ለማድረግ ወሳኝ ሚና አለው ብለዋል። የኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በርን የማግኘት ፍላጎትም ከታሪክ፣ ጂኦግራፊና ቀጣናዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የሚያያዝ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ኮሞዶር ተገኝ ለታ፥ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብሔራዊ ተጠቃሚነት ከዓባይና ከቀይ ባሕር ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው ብለዋል። ከበርካታ ዓመታት በፊት ፈርሶ የነበረውን የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል መልሶ በማደራጀት በሰው ኃይል፣በአደረጃጀት፣በቴክኖሎጂ አስተማማኝና ጠንካራ ሠራዊት እየተገነባ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በመድረኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፣የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች፣የመከላከያ ሠራዊት መኮንኖችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
በኮምቦልቻ ከተማ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ተኪ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ እየተደረገ ነው
Oct 18, 2025 38
ኮምቦልቻ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፡-በኮምቦልቻ ከተማ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ተኪና የውጭ ንግድ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ እየተደረገ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ገለጹ። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በኮምቦልቻ ከተማ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የሥራ እንቅስቃሴ እየጎበኙ ነው። የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድ አሚን የሱፍ በገብኝቱ ላይ እንደገለጹት፤ በከተማው የአምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ተኪና የውጭ ንግድ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ እየተሰራ ነው። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ባለሃብቶች የሚገጥሟቸውን ችግሮች መፍታት መቻሉንም አንስተዋል። በዛሬው ጉብኝት ላይ የሚሰጡ አስተያየቶችን እንደ ግብአት በመጠቀም ከተማዋን ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ተመራጭ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራም ገልጸዋል። በጉብኝቱ ላይ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ እንድሪስ አብዱን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል ሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
በዞኑ ከ42 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ለማልማት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተካሄደ ነው
Oct 18, 2025 41
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፡- በአዊ ብሔረሰብ ዞን በነባርና አዲስ የመስኖ አውታሮች 42ሺህ 123 ሄክታር መሬት ለማልማት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተካሄደ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በበጋው ከሚለማው ከዚሁ መሬት ሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ቤዛዊት ጌታሁን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የመስኖ ልማትን በማስፋፋት በምግብ ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው። በዚህም በዘንድሮ የበጋ ወቅት አርሶ አደሮችን በመደገፍ 42 ሺህ 123 ሄክታር መሬት በነባርና በአዲስ መስኖ ለማልማት ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥ 28ሺህ ሄክታሩ የስንዴ ልማት የሚሸፈን መሆኑን ጠቅሰው፤ ወደ ዘር ስራ ለመግባት አርሶ አደሩን በኩታ ገጠም የማደራጀት፣ የመሬት ልየታና የእርሻ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በስንዴ ከሚለማውም ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቀዋል። ቀሪው መሬት የሚለማው ሽንኩርትን ጨምሮ በተለያየ አትክልት መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ በመስኖ ከሚለማው መሬት ውስጥ ከሁለት ሺህ 500 በላይ ሄክታር በማረስና በማለሳለስ ለዘር ዝግጁ ተደርጓል ብለዋል። የበጋ መስኖ ልማቱን በኩታ ገጠም አሰራርን በመጠቀምና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ ከዚህ ቀደም በሄክታር 37 ኩንታል የነበረው ምርታማነት ወደ 41 ኩንታል ለማሳደግ ግብ መያዙን አንስተዋል። በዞኑ ባለፈው ዓመት ከ20 ሽህ 700 በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ብቻ በማልማት ከ768 ሸህ ኩንታል በላይ ምርት ማግኘት መቻሉን ከግብርና መምሪያው የተገኘ መረጃ ያስረዳል።
የሌማት ትሩፋትና የከተማ ግብርና መርሀግብሮች ከተረጂነት ወደምርታማነት ለመሻገር የሚደረገውን ጥረት እያገዙ ነው
Oct 18, 2025 42
አርባ ምንጭ፣ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ):-በአርባ ምንጭ ከተማ የሚከናወኑ የሌማት ትሩፋትና የከተማ ግብርና መርሀግብሮች ከተረጂነት ወደምርታማነት ለመሻገር የሚደረገውን ጥረት እያገዙ መሆኑን የከተማው ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ መተኪያ አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሀገር አቀፍ ደረጃ የሌማት ትሩፋትና የከተማ ግብርና መርሀግብሮችን ማስጀመራቸውን ተከትሎ በከተማው ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ ነው። በልማቱም የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎችና የተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በስፋት እየተሳተፉ መሆናቸውን ገልጸው፣ በመርሀግብሮቹ ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ተናግረዋል። መርሀግብሮቹ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥና የአመጋገብ ሥርአትን ከመቀየር ባለፈ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ አቅም በማሳደግ ከተረጂነት ወደምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት እያገዙ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ በወተት ላሞችና በዶሮ እርባታ፣ በንብ ማነብ እንዲሁም በጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ውጤታማ ናቸው ብለዋል። በዘርፉ የተሠማሩ አካላትን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በአስተዳደሩ በኩል የመስሪያ ቦታና የገንዘብ ብድር አገልግሎት እንዲሁም የገበያ ትስስርና ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም አቶ መተኪያ አስረድተዋል። በከተማው በሌማት ትሩፋት ትግበራ ከተሳተፉ ወጣቶች መካከል "ነህሚያ የእንስሳት እርባታ ማህበር" ሰብሳቢ ህዝቅኤል ኦሎባ፣ ከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸላቸው የቦታና የገንዘብ ብድር ካለፈው ዓመት አጋማሽ ጀምሮ ማህበሩ ወደስራ መግባቱን ተናግሯል፡፡ በእንስሳት እርባታ ሥራ ውጤታማ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የወተት ምርታቸውን ለተጠቃሚው ማቅረብ መጀመራቸውን ገልጿል፡፡ የ"አዲስ ዓለም" የዕንቁላል ዶሮ እርባታ ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ታምራት እንዳለ በበኩሉ እንደገለጸው በ2016 በማህበር ተደራጅተው ከ270 በላይ እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማርባት ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግሯል፡፡ ትምህርት ቤቶችም ከመማር ማስተማር ሥራ ጎን ለጎን በከተማ ግብርና የጓሮ አትክልት በማልማት የውስጥ ገቢያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የከተማው ትምህርት መምሪያ ሃላፊ አቶ መለሰ መንዛ ናቸው። እያንዳንዱ ትምህርት ቤት በከተማ ግብርና ሥራ በዓመት እስከ 700 ሺህ ብር በማግኘት የውስጥ ገቢውን ከማሳደግ ባለፈ ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችል አቅም መፍጠሩን ተናግረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በአፍሪካ ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ ይገባል
Oct 17, 2025 124
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ዘላቂና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ። ከጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 2ኛው የአፍሪካ የክህሎት ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) መርሃ ግብሩ፣ በአፍሪካ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠናን ጥራት ለመጠበቅና ተደራሽነቱን ለማስፋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ምርጥ ተሞክሮ ያካፈለችበት እና ከሌሎች ልምድ የወሰደችበት ስኬታማ መድረክ እንደነበርም ገልጸዋል። የአፍሪካ መጻዒ እድል የሚወሰነው በወጣቶች ላይ በምንሰራው ሁሉን አቀፍ የክህሎት ልማት ስራ ልክ ነው ሲሉም ገልጸዋል። በአፍሪካ ዘላቂና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግ እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለሰው ሀብት ልማት ስራ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች እንደምትገኝ ጠቁመው፤ በቀጣይም ከአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ጋር በማስተሳሰር አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቀዋል። በመድረኩ ማጠቃለያም የአፍሪካ አገራት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሀብት ለማፍራት በጋራ የሚሰሩበት አቅጣጫ መቀመጡንም አመላክተዋል። በአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋስፓርድ ዳንያንክምቦና በበኩላቸው፤ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት የእድገት ማሳለጫ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም የአፍሪካ አገራት በአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ መሰረት ቅንጅት በመፍጠር ዘርፉን በማሳደግ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ የዛሬ የአፍሪካ ወጣቶች ነገን ፈጠራ በታከለበት ሁኔታ መምራትና ለውጥ የማምጣት ሃላፊነት እንደተጣለባቸው አንስተው፤በዚህ ሒደት ውስጥ ከጎናቸው እንደሚሆኑ አረጋግጠዋል፡፡ ከኢኳቶሪያል ጊኒ የመጡ የመድረኩ ተሳታፊ ዮላንዳ አሱሙ በበኩላቸው፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የክህሎት ሳምንት በርካታ ልምዶችን የተለዋወጥንበት ነበር ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ሁለተኛው ክህሎት ሳምንት እጅግ አስተማሪና ትልቅ ግንዛቤ የወሰድንበት ሆኖ አልፏል ያለው ደግሞ ከሴኔጋል የመጣው ወጣት ደቪድ ሞዓድ ነው፡፡
ለዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሚያስፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል የማፍራት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 17, 2025 74
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፡-በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ለሚፈጠሩ የስራ እድሎች የሚያስፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል የማፍራት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የስራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር"የነገው የስራ ዓለም"በሚል መሪ ሃሳብ ቀጣሪ ድርጅቶችን እና ተመራቂ ተማሪዎችን ለማገናኘት ያዘጋጀው አውደ ርዕይ እየተካሄደ ነው። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታው ሰለሞን ሶካ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ የነገው የስራ ዓለም ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ከወዲሁ ዝግጅት እየተደረገ ነው። ዘርፉ የሚፈልገውን የሰው ኃይል ለማዘጋጀት ገበያ መር የክህሎት ልማት እና ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ዜጎች ወደፊት በሚኖሩ የስራ እድሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ መንግስት የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በኢትዮጵያ የተማሩ ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ ሰፋፊ የስራ እድሎችን ለመፍጠር ሁለንተናዊ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን ገልፀዋል። የመንግስትና የግሉን ዘርፍ ትብብርና አጋርነትን መሰረት ያደረጉ የስራ ስምሪቶችን በማስፋት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። አውደ ርዕይውን በትብብር ያዘጋጀው አፍሪ ወርክ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ስመኝ ታደሰ በበኩላቸው፥ አውደ ርዕዩ በቀጣይ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚኖሩ የስራ እድሎች ቀድሞ ዝግጅት በሚደረግባቸው መስክ ላይ ለመወያየት ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም ወጣቱ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን መሰረት ካደረጉ ቴክኖሎጂዎች ጋር እንዲተዋወቅ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት የተዘጋጀ መሆኑን ነው የገለጹት። ቀጣሪ ድርጅቶችን ወክለው የተገኙት እሌኒ አምሀ እና ቤቴል ተስፋዬ በበኩላቸው አውደ ርዕዩ ከተለያዩ ድርጅቶች፣የስራ እድል ከሚፈልጉ ዜጎችንና ባለድርሻ አካላት ጋር በቀጥታ ለመገናኘት ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ስራ በመፍጠር ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ስራ መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።
በኢትዮጵያ 100 ከተሞችን ተደራሽ የሚያደርግ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ተግባራዊ ሊደረግ ነው
Oct 17, 2025 90
ጎንደር ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ 100 ከተሞችን ተደራሽ የሚያደርግ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ፕሮጀክት ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ ኢንስቲትዩቱ ጎንደር ከተማን የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ፕሮጀክት የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ዛሬ ተፈራርሟል፡፡ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሐይ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያን ታላላቅ ከተሞች ዘመኑን የዋጀ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡ ኢንስቲትዩቱ በ10 ዓመት ውስጥ 100 ከተሞችን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ስራ መግባቱን ጠቁመው በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ የክልል ከተሞችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል፡ በአማራ ክልል የደብረ ብርሃንና የኮምቦልቻ ከተሞች የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተው፤ በደሴና ወልዲያም ፕሮጀክቱን ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ የከተሞች የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ከተሞች ወደ ስማርት ሲቲ የሚያደርጉትን የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያፋጥን ከመሆኑም በላይ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ ለሆኑ ከተሞች የላቀ አበርክቶ አለው፡፡ ዲጂታል የአድራሻ ስርዓት መኖሪያ ቤቶችን፣ መንገዶችንና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያሉበትን መገኛ ቦታ ርቀትና አቅጣጫ በቀላሉ ለማመልከት የሚያስችል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንደሆነም አብራርተዋል፡፡ ዲጂታል የአድራሻ ስርዓት ለከተሞች ፈጣን እድገትና ለውጥ ቁልፍ የቴክኖሎጂ መሳሪያ ነው ያሉት የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው፡፡ የጎንደር ከተማ ሰባት ታላላቅና ታዋቂ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች እንዳሏት ጠቅሰው፤ እነዚህን የቱሪዝም የመስህብ ሀብቶች በማስተዋወቅ ቱሪስቶች ስፍራዎቹን በቀላሉ እንዲጎበኙ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ቴክኖሎጂ ነው ብለዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ለፕሮጀክቱ ተፈጻሚነት ከኢንስቲትዩቱ ጋር በቅርበት የሚሰራ ሲሆን በመጪው ጥር ወር በከተማው በድምቀት ለሚከበረው የጥምቀት በዓል ቴክኖሎጂውን ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የኢንስቲትዩቱ የስራ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች ተገኝተዋል፡፡
በተያዘው በጀት ዓመት ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ስማርት ቴክኖሎጂዎችን ለደንበኞች ለማቅረብ ዝግጅት ተደርጓል - ኢትዮ ቴሌኮም
Oct 17, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በተያዘው በጀት ዓመት ከ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ስማርት የአገልግሎት ማሳለጫ ቴክኖሎጂዎችን ለደንበኞች ለማቅረብ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። የኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተደራሽነትን ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ዘኔክሰስ የተሰኘ አገልግሎት በይፋ አስጀምሯል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ፥ የኢትዮጵያን ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እውን ለማድረግ ኢትዮ ቴሌኮም ለቴሌኮምና ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታ ትኩረት መስጠቱን ተናግረዋል። ባለፉት ስድስት ዓመታትም የአራተኛውና አምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ አገልግሎት፣ ክላውድ፣ የቴሌብርና ዘመን ገበያን ጨምሮ ሥራ ላይ የዋሉ መሰረተ ልማቶች ትልቅ አቅም እየፈጠሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። የደንበኞችን ቁጥር ወደ 100 ሚሊዮን ለማድረስ ግብ መጣሉን ገልጸውም ከዚሁ ውስጥ 69 ሚሊዮን ደንበኞች የሞባይልና ብሮድባንድ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ለማድረግ ስትራቴጂ ተነድፎ ወደ ሥራ መገባቱን አብራርተዋል። በኢትዮጵያ 85 ነጥብ 9 ሚሊዮን የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች እንዳሉ አመልክተው፤ ከእነዚህ ውስጥ 47 ሚሊዮኑ ብቻ ኢንተርኔትን እንደሚጠቀሙ አስታውቀዋል፡፡ ለዚህም የተለያዩ ምክንያቶች ቢኖሩም የመጠቀሚያ ስማርት መሳሪያዎች ዋጋ መወደድ ዋነኛው ምክንያት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ዘ ኔክሰስ የተሰኘ አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ የክላውድ ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ የእጅ ስልኮች፣ ላፕቶፖች፣ ታብሌቶችና ወርክ ስቴሽኖች በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ማቅረቡን ተናግረዋል። መሳሪያዎቹን የሚጠቀሙ ደንበኞች የኢትዮ ቴሌኮምን ክላውድ በቀጥታ በመጠቀም አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸው መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ስማርት ቴክኖሎጂዎችን ለማቅረብ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው ይህም የኢንተርኔት ተደራሽነትን በከፍተኛ ሁኔታ ያሻሽላል ነው ያሉት። በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት፣ ትምህርትን ጨምሮ የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶች በኢንተርኔት እንደሚሰጡ ጠቁመው፤ በዚህ ረገድ ዘ ኔክሰስ አገልግሎት ወደ ስራ መግባት ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡ ዘኔክሰስ አገልግሎት ተቋማትን ተወዳዳሪ ለማድረግ እንዲሁም ቀልጣፋ ዘመናዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ እንዲያደርጉ ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም አስረድተዋል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጀመራል
Oct 18, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦ የ2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ጅማሮውን ያገኛል። ሊጉ በሁለት ምድቦች ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን በእያንዳንዱ ምድብ 10 ክለቦች ይገኛሉ። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ፣ ፋሲል ከነማ ስሑል ሽሬ፣ መቻል፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ ወላይታ ድቻ ፣ሃዋሳ ከተማ፣ መቀሌ 70 እንድርታ፣ ሲዳማ ቡና እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በምድብ አንድ የሚገኙ ቡድኖች ናቸው። በምድብ ሁለት ነገሌ አርሲ፣ ኢትዮጵያ ቡና፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ፣ ባህር ዳር ከተማ፣ አዳማ ከተማ፣ ሸገር ከተማ፣ ኢትዮጵያ መድን፣ ሀድያ ሆሳዕና፣ አርባምንጭ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተደልድለዋል። የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ዘጠኝ ሳምንታት ውድድር በአዲስ አበባ እና ሃዋሳ ከተሞች ይካሄዳሉ። በዚሁ መሰረት የመጀመሪያ ሳምንት አራት ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሸገር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት፣ ነገሌ አርሲ ከአርባምንጭ ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከሲዳማ ቡና ከቀኑ 9 ሰዓት እና ድሬደዋ ከተማ ከሃዋሳ ከተማ ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በድሬደዋ ሊደረጉ የነበሩ የሊጉ የመጀመሪያ ዘጠኝ ሳምንታት ጨዋታዎች ከተማዋ ውድድሩን ለማስተናገድ ዝግጁ አለመሆኗን ማሳወቋን ተከትሎ ምክንያት ወደ ሃዋሳ መዘዋወራቸው የሚታወስ ነው። የመጀመሪያ ሳምንት መርሃ ግብር እስከ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። 20ዎቹ ክለቦች በ38 የውድድር ሳምንታት 380 ጨዋታዎችን እንደሚያደርጉ የሊጉ አክሲዮን ማህበር መረጃ ያመለክታል።
የሊጉ መሪ አርሰናል ከፉልሃም ጋር ይጫወታል
Oct 18, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከዓለም አቀፍ ጨዋታዎች በኋላ በስምንተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ ይመለሳል። ፉልሃም ከአርሰናል ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። የምዕራብ ለንደኑ ፉልሃም በስምንት ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። የሰሜን ለንደኑ አርሰናል በ16 ነጥብ የሊጉ መሪ ነው። አርሰናል ካሸነፈ ከተከታዩ ሊቨርፑል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ከፍ ያደርጋል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ማንችስተር ሲቲ ከኤቨርተን፣ ብራይተን ከኒውካስትል ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ ከቦርንማውዝ፣ በርንሌይ ከሊድስ ዩናይትድ እና ሰንደርላንድ ከዎልቭስ በተመሳሳይ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ ኖቲንግሃም ፎረስት ከቼልሲ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።
በኦሮሚያ ክልል የስፖርት መሰረተ ልማትን በማስፋፋት የዘርፉን እድገት ለማስቀጠል እየተሰራ ነው
Oct 17, 2025 82
አዳማ ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የስፖርት መሰረተ ልማትን በማስፋፋት የዘርፉን እድገት ለማስቀጠል እየተሰራ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ ገለፁ። 20ኛው የኦሮሚያ ክልል ስፖርት ምክር ቤት ጉባኤ ''ስፖርት ለሀገር ማንሰራራት'' በሚል መሪ ሃሳብ የፌዴራል እና የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተካሄዷል። የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለፁት በክልሉ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ከዚህ ውስጥ አንዱ የስፖርት መሰረተ ልማት ዝርጋታ መሆኑን ጠቅሰው የክልሉ መንግስት በዚህ ረገድ ትልቅ ስራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። በዚህም በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በበርካታ አካባቢዎች የወጣቶች ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የስፖርት አካዳሚዎች ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል ብለዋል። የተሰሩት ስራዎችም የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ የሚያግዙ ከመሆናቸውም በላይ ወጣቶች በመልካም ስብዕና እንዲታነጹ እና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ እድል እየፈጠሩ መሆኑን አውስተዋል። እስካሁን የተከናወኑ የስፖርት መሰረተ ልማት ስራዎች አበረታች ቢሆኑም አሁንም ልዩ ትኩረት የሚፈልግ ጉዳይ በመሆኑ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ማደግ አለበት ብለዋል። የኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ቢያ በበኩላቸው ክልሉ የሀገር ባለውለታ የሆኑ ስፖርተኞችን ለሀገር ያበረከተ ነው ብለዋል። የክልሉ የስፖርት ዘርፍ ጠንካራ መሰረት እንዲኖረው እና ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የሚሰሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በቀጣይም አዳዲስ የአትሌቲክስ ክለቦችን ለማደራጀትና ለማጠናከር የሚያስችሉ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች እንደሚተገበሩም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው ተሸነፈ
Oct 13, 2025 354
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ከቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገው ጨዋታ 3 ለ 1 ተሸንፏል። ማምሻውን በኦገስት 4 ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ተቀይሮ የገባው ፒዬር ላንዲ ካቦሬ በ64ኛው፣ በ82ኛው እና በ96 ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ቢኒያም አይተን በ84ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ በምድብ አንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ በዘጠኝ ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ቡርኪናፋሶ በ21 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ምርጥ ሁለተኛ ሆኖ በጥሎ ለማለፍ ከሚሳተፉ አራት የአፍሪካ ሀገራት አንዷ የመሆን እድሏን አስፍታለች። በዚሁ ምድብ ማምሻውን በተደረገው ጨዋታ ግብጽ ጊኒ ቢሳውን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ለዓለም ዋንጫ ያለፈው ቡድኑ በ26 ነጥብ ምድቡን በመሪነት አጠናቋል። በዚሁ ምድብ በተደረገው ጨዋታ ሴራሊዮን ጅቡቲን 2 ለ 1 አሸንፋለች።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ ናት- ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)
Oct 16, 2025 155
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርኃ ግብር አካሂዷል። በመርኃ ግብሩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያሥላሴ፣ ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተገኝተዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ምላሽ ለመስጠት ያለንን ቁርጠኝነት ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። ጉባዔው አፍሪካውያን ለአየር ንብረት ለውጥ ተጨባጭ መፍትሔዎችን በመውሰድ ግንባር ቀደም መሆናቸውን ለዓለም በማሳየት ስኬታማ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም ለጋራ ችግሮች በጋራ ምላሽ ለመስጠት አቅማቸውን ያጠናከሩበት እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ይህን ስኬት ተጠቅሞ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት የሥራ ዕድል ፈጠራ ውጤታማ ተግባር እያከናወነች ትገኛለች
Oct 16, 2025 121
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል በአፍሪካ ግንባር ቀደም የሆነ ተግባር እያከናወነች መሆኑ ተገለጸ። ይህ የተገለጸው "አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችና ወጣቶች" በሚል ርዕስ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የተጠና ጥናት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ይፋ በሆነበት መድረክ ላይ ነው። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት እና የጥናቱ መሪ ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና እንደገለጹት የአረንጓዴ ልማት ስራ ዕድል ፈጠራ የአካባቢን ዘላቂነት ከማረጋገጥ ባሻገር ለወጣቶች ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል ወሳኝ ሚና አለው። ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የአካባቢ ጥበቃን በማጠናከር ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር በአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ተግባር እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይ በአረንጓዴ ልማት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል በሁሉም ሴክተሮች በማስፋት የወጣቱን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማትን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል። በመሆኑም በተለይ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የአረንጓዴ የስራ ዕድል የሚፈጥሩ ስልጠናዎች ተገቢ ትኩረት እንዲያገኙ እንዲሁም በፖሊሲዎች ውስጥ ልዩ ትኩረት እንዲሰጣቸው በማድረግ ሊበረታቱ እንደሚገባም አመልክተዋል። የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለበል ደሴ በበኩላቸው፣ ጥናቱ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ዕድገት ስትራቴጂዎችና የወጣቶች የሥራ ስምሪት ዕቅዶችን እንደሚደግፍ ጠቅሰዋል። ግኝቶቹ ወደ ተግባራዊ ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞች እንዲተረጎሙ ከሚመለከታቸው የመንግስት መሥሪያ ቤቶች እና የልማት አጋሮች ጋር በቀጣይ እንደሚሰራበት ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የአካባቢ ጥበቃን የሚያጠናክር አረንጓዴ ሥራዎች ሙያዊ ሥልጠና ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የአካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ገነነ አበበ(ዶ/ር) ናቸው። በቀጣይ የአረንጓዴ ሥራን ይበልጥ ለማስፋፋት በተለይ በቀጣሪ መሥሪያ ቤቶችና ሌሎች ተቋማት ላይ የግንዛቤ ሥራ ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርትን በማስፋት ረገድ በአፍሪካ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች ነው
Oct 15, 2025 220
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም ለአረንጓዴ ትራንስፖርት መስፋፋት በአፍሪካ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። "በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የትራንስፖርት ስርዓትን ማረጋገጥ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ የጀመረው የ2025 የአፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ሳምንት የመክፈቻ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡ መድረኩ ለአህጉሪቱ ዘላቂ ትራንስፖርት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስፋፋት ለአየር ንብረት የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ቁልፍ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ፣ በአከባቢ ጥበቃ ብሎም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማስፋፋት አረንጓዴ የትራንስፖርት ስርዓትና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ እየገነባች እንደምትገኝም ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ አበረታች የፖሊሲ ማዕቀፍ በማዘጋጀት የትራንስፖርት ምህዳሯን በመሠረታዊነት እየቀየረች መሆኑንም ጠቁመዋል። በጋራ አቅም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የማምረት፣ የኃይል መሙያ መሠረተ ልማትን ማስፋፋት እንዲሁም ቀጣናዊ የተቀናጁ የእሴት ሰንሰለቶችን መፍጠር እንደሚቻል አመልክተዋል። አፍሪካ ቴክኖሎጂዎችን በራሷ አቅም ለማልማት ትልቅ ትኩረት መስጠት እንዳለባት ጠቁመው፥ በትራንስፖርት ዘርፉ ዘላቂ ለውጥን ማምጣት የሚያስችል ፈጠራ ላይ የተመሰረተ የተሻለ ነገን ልንቀርጽ ይገባል ብለዋል። የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን፣ የሀገሪቱን የታዳሽ ኃይል አቅም መጠቀም የሚችል የትራንስፖርት ዘርፍ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ማስፋፋት የሰጠችው ከፍተኛ ትኩረት እውቅና እንደተሰጠው አመላካች መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስትራቴጂ በማጽደቅ ወደ ትግበራ ማስገባቷን ገልጸዋል፡፡ መንግሥት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ ባደረገው የቀረጥ ማበረታቻ ምክንያት በርካታ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እየገቡ መሆኑን አስታውቀዋል። ጉባዔው የአፍሪካ ሀገራትን የብሉ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥበትም ተጠቁሟል፡፡
ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች ነው
Oct 13, 2025 272
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ገለጹ፡፡ በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በአረንጓዴ ትራንስፖርትና በታዳሽ ኃይል ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች የአዳማ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን፣ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰንን ጨምሮ ከኢትዮጵያ እና ኬንያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ኩባንያዎች ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴዔታ በርኦ ሀሰን በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የትራንስፖርት ዘርፉን ጨምሮ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ ባከናወነቻቸው ተግባራት በርካታ ለውጦችን አስመዝግባለች ብለዋል፡፡ ለዚህም በሕዳሴ ግድብ፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብርና በንፋስ ኃይል ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ትልቅ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዘርፉን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅና ከአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የጸዳ እንዲሆን ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡ መንግሥት ታዳሽ ኃይል የሚጠቀም የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍን እውን ለማድረግ ጠንካራ የፖሊሲ ድጋፍ ስለማድረጉ አንስተዋል። በዚህም በርካታ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በማንሳት፥ ባለሀብቶችም በዘርፉ ኢንቨስት እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና መንግስት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓት የተሰማሩ ተቋማትን እንደሚያበረታታ አረጋግጠዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለዓለም ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ናቸው ብለዋል፡፡ በተለይ ደግሞ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ የወሰደው እርምጃ ይበል የሚባል ነው ብለዋል፡፡ ሀገራቸው ይህንን ተግባር እንደምትደግፍም አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ሳምንት ከነገ ጥቅምት 4 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 6 ቀን 2018 በአዲስ አበባ ይካሔዳል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ የብዙሃን ትራንፖርት፣ ባቡር፣ ኮሪደር ልማት፣ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች እንዲሁም በፖሊሲ ረገድ እያከናወነች ያለችውን ተጨባጭ ሥራ እንደምታቀርብም ተገልጿል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ
Oct 15, 2025 250
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር እና በአህጉሪቷ የማካካሻ ፍትህን ለማረጋገጥ በበለጠ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን በአፍሪካ ደረጃ ዛሬ በአህጉሪቷ መዲና አዲስ አበባ ዛሬ ይከበራል። “የገጠር ሴቶችን በማካካሻ ፍትህ አማካኝነት ማብቃት፤ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ስርዓተ ምግብን ማረጋገጥ” የቀኑ መሪ ሀሳብ ነው። በቀኑ አከባበር ላይ የአፍሪካ ህብረት አመራሮች፣ የመንግስታት ተወካዮች፣ የገጠር ሴቶች አመራሮች እና ተወካዮች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ የዳያስፖራ ተወካዮች፣ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ይሳተፋሉ። የቀኑ አከባበር አካል የሆነ የቴክኒክ ውይይት ትናንት የተካሄደ ሲሆን የአፍሪካ የገጠር ሴቶች መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ባለሙያዎች ሴቶችን ለማብቃት በየሀገራቱ እየተተገበሩ ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ የእውቀት እና የተሞክሮ ልውውጥ አድርገዋል። ዛሬ በሚኖረው ዋናው የቀኑ አከባበር የከፍተኛ ባለስልጣናት ቁልፍ ንግግሮች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የገጠር ሴቶች ኢኒሼቲቭ የተሞክሮ ማጋራት መርሃ ግብሮች እና አውደ ርዕዮች ይካሄዳሉ። ሁነቶቹ የገጠር ሴቶች በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እና በግብርና መካናይዜሽን አማካኝነት የሚበቁባቸው የኢኖቬሽን አማራጮች የሚቀርቡባቸው ናቸው። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን ከአፍሪካ ህብረት የ2025 መሪ ሀሳብ ከሆነው “የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” የተሳሳረ መሆኑ ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የማሻሻሻ ፍትህ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አካሄድ መሆኑን አመልክቷል። የቀኑን አከባበር ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የጋራ መግለጫው አፍሪካ ስርዓተ ጾታን ባማከለ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ስራ፣ የገጠር ሴቶችን በማብቃት እንዲሁም ማካካሻ ፍትህ እኩልነት የተረጋገጠበትና የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመገንባት ያላትን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት እንደሆነ ተገልጿል። የዓለም የገጠር ሴቶች ቀን የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማረጋገጥ እና በማካካኛ ፍትህ አማካኝነት በገጠሪቷ የአፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። ህብረቱ ቀኑን ሲያከብር የበለጸገች፣ ሁሉን አቃፊ እና ዘላቂነትን ያረጋገጠች አህጉር ለመገንባት ባለው መሻት ውስጥ ሴቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ወደኋላ እንዳይቀሩ ዳግም ቃል ኪዳኑን የሚያድስበት እንደሆነ አመልክቷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እ.አ.አ በ2007 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ባፀደቀው የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 62/136 አማካኝነት ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን እ.አ.አ ኦክቶበር 15 እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ በገጠር የሚገኙ ሴቶች ለግብርና፣ ምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ዘላቂ ልማት ያላቸው ወሳኝ አበርክቶዎች የሚዘከርበት ነው።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በሙሉ አቅም መተግበር ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው - መሐመድ አሊ ዩሱፍ
Oct 10, 2025 395
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ሙሉ ለሙሉ ገቢራዊ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁነቶች በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት እና ተወዳዳሪነት ተጽእኖ እያሳደሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከመቼው ጊዜ በላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ ለሙሉ በአፋጣኝ መተግበር እንደሚገባው የሚያመላክት ነው ብለዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ከቀረጥ ጋር ያልተያያዙ የንግድ ገደቦችን በማንሳት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተሳለጠ የንግድ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችሉ ማዕቀፎችን በመተግበር ለአጀንዳ 2063 መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኮሜሳ፣ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳዴቅ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) የሶስትዮሽ ትብብር ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕቀፉ የትስስር አጀንዳ ተምሳሌት እና አንድ የሆነች፣ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች አህጉር ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ቀጣናዊና አህጉራዊ የትስስር አጀንዳዎችን ትግበራ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንደሚያጠናክሩ ገለጹ
Oct 10, 2025 364
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን የቆየ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። ጀርመን ለኢጋድ ቀጣና የተለያዩ የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፎችንም ይፋ አድርጋለች። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በልማት ትብብራቸው ዙሪያ በጅቡቲ ስትራቴጂካዊ ምክክር አድርገዋል። በምክክሩ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ሚኒስቴር የምስራቅ አፍሪካ ዘርፍ ኃላፊ ሃኒንግ እና በጅቡቲ የጀርመን አምባሳደር ሄይከ ፉለር (ዶ/ር) ተገኝተዋል። ስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ የግንኙነት ማዕቀፎች ላይም መክረዋል። ፍልሰት እና አየር ንብረት ለውጥ የውይይቱ አበይት ማጠንጠኛዎች ናቸው። ሁለቱ ወገኖች የጀርመን ቀጣናዊ የፍልሰት ፈንድ ዳግም ማዋቀር ሂደት መልካም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በማንሳት የኢጋድ የቀጣናዊ የፍልሰት ፖሊሲ ማዕቀፍ ፣ የነጻ እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፎች እና የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ የማጠናከር ስራ ለመደገፍ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ጀርመን ለኢጋድ የፍልሰት ፖሊሲ ትግበራ ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ ትግበራ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ ቃል መግባቷን ኢዜአ ከቀጣናዊ ተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም ጀርመን በኢጋድ አባል ሀገራት ለሚከናወኑ የማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ስራዎች በቀጣናዊ የአደጋ ፋይናንስ ፕሮግራም አማካኝነት 22 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ መዘጋጀቷ ተመላክቷል። የፋይናንስ ማዕቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ድንገተኛ አደጋዎችን የመከላከል ስራዎች የሚደገፍ እና የኢጋድ የድርቅ አደጋን የመቋቋም እና ዘላቂነት ኢኒሼቲቭ ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን የሚደግፍ ነው። በስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች ውጤት ተኮር፣ አሳታፊ እና ተጠያቂነትን መሰረት ያደረገ አጋርነትን መፍጠር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢጋድ እና ጀርመን ትብብራቸውን ለማጠናከር፣ የጋራ ስራዎቻቸው የአባል ሀገራት የቅድሚያ ትኩረቶች ያማከሉ እንዲሆኑና የፖሊሲ ምክክራቸውን በመደበኛነት ለማከናወን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ኢጋድ እና ጀርመን 37 ዓመታትን ያስቆጠረ አጋርነት እንዳላቸው መረጃዎች ያመለክታሉ።
የአፍሪካ ህብረት የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 7, 2025 435
አዲስ አበባ፤ መስከረም 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷ ወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት ዲያላ ሞሙኒ እና አህመድ ቤኒንግ ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። የአፍሪካ ህብረት የወጣቶች ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ሊቀ መንበር ኡቺዚ ምካንዳዋየር በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል። የአፍሪካ ህብረት ስምምነቱ የአህጉሪቷ ወጣቶች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና ወጣቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። በስምምነቱ አማካኝነት የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት በሀገራት ደረጃ ያሉ የወጣት ምክር ቤቶች የሚያቀናጅ አህጉራዊ ማዕቀፍ እና ለአፍሪካ ወጣቶች እንደ ጋራ ድምጽ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ንቅናቄ የወለደው አህጉራዊ አደረጃጀት ሲሆን እ.አ.አ በ1962 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በጊኒ ኮናክሪ ባደረጉት ስብስባ ህብረቱን አቋቁመዋል። ህብረቱ የተመሰረተው በወቅቱ ወጣቶች አፍሪካ ከቅኝ ግዛት እንድትላቀቅ ለነበረው ትግል አቅም እንዲሆኑ ከማሰብ የመነጨ ነው። የወጣቶች ህብረቱ እንቅስቃሴ የፖለቲካ ድጋፍን በማሰባሰብ እና የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዲወጡ በማድረግ ረገድ ስትራጂካዊ ሚናውን ተጫውቷል። የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እ.አ.አ በ2006 ባደረገው ስብስባ የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በድጋሚ የማደራጀት የውሳኔ ሀሳብ በማፅደቅ ህብረቱ የአህጉሪቷ የወጣት መዋቅር እንዲሆን በይኗል።
ሐተታዎች
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 241
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 409
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 608
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
"ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 694
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ። አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው። ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል። ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡ ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 989
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1726
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2528
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2685
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 308
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 305
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6161
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4640
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 772
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡ በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!
በትግራይ ክልል የመስቀል በዓል አከባበር
Sep 27, 2025 792
የመስቀል በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በልዩ ድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ ነው። በዓሉ እንደየአካባቢው ባህላዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። በትግራይ ክልልም የመስቀል በዓል እንደሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሁሉ በናፍቆት ከሚጠበቁና በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት ተርታ ይመደባል። ለዚህም ሲባል የተለያዩ ዝግጅቶች ከበዓሉ ዋዜማ በፊት እንዲጠናቀቁ የሚደረግ ሲሆን፥ በተለይ በየዓመቱ መስከረም 16 እና 17 ዘመድ አዝማድ ተጠራርተው የሚገናኙበት የፍቅርና የአብሮነት በዓል ሆኖ ይከበራል። የክርስቶስ ግማደ መስቀል በንግስት ኢሌኒ አማካኝነት መገኘቱን በማሰብ በየዓመቱ መስከረም አጋማሽ ላይ የሚከበረው የመስቀል በዓል የመስቀል ኃያልነት፣ እውነት በተደበቀበት ለዘላለም እንደማይቀርና ፍቅርን አብዝቶ የሚሰበክበት ከዚህ ባለፈም እርቅ የሚወርድበትና ደስታ የሚገለጽበት አጋጣሚ መሆኑም ይገለጻል። በትግራይ የበዓሉን ታላቅነትና ክብር ለማድመቅ ምእመናን ጽዱ ልብስ ለብሰውና የተለያዩ ዝማሬዎችን በማሰማት ደመራ ወደሚደመርበት ሥፍራ ችቦ ይዘው በመሄድ ደምራውን በማቀጣጠል የሚያከበሩት ሲሆን፣ በእለቱ የቤት እንስሳት ጭምር ቀንዳቸውና ጀርባቸው ላይ ቅቤ ተቀብተው እንዲያርፉ ይደረጋል። ዘመድ አዝማድ፣ ጎረቤታሞች፣ አብሮ አደጎችና የበዓሉ ታዳሚ እንግዶችም ተሰባስበው ማለዳ ላይ ገንፎ በማዘጋጀት ይመገባሉ። የእንስሳት እርድ በማከናወን ባህላዊ መጠጦችን በማዘጋጀት በዓሉን የፍቅር፣ የመሰባሰብ፣ የአንድነትና ተካፍሎ የመብላት በዓል መሆኑን በተግባር የሚያሳይበት ክስተት ሆኖ ያልፋል። "ዓኾይ ዓኾኾይ" የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ በማለትም ችቦ ተሎኮሶ በየቤቱ በመዞር የምረቃ እና ለሚቀጥለው ዓመትም በሰላምና ደስታ እንዲሁም እድሜና ጤናን በመመኘት ይከወናል። የአደባባይ በዓል የሆነው የመስቀል በዓል በዝማሬ፣ በሆታና እልልታ የሚገለጽ ሲሆን፤ ወርሃ መስከረም እሸት አሽቶ አበቦች አብበውና ምድር ልዩ ልምላሜን ተላብሶ የሚታይ በመሆኑ ልክ በታሪኩ እንደሰፈረው የሰላም፣ የእውነትና የአንድነት በዓል መሆኑን በተግባር የሚታይበት ነው።