አርእስተ ዜና
የሀገር ውስጥ ምርቶችን መጠቀምን ሁሉም ባህል ማድረግ አለበት - የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
Jul 14, 2025 51
  አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓትን በማሳለጥ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ባህልን ማጎልበት እንደሚገባ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) ገለጹ ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ያዘጋጀው 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛር ተከፍቷል።   ኤግዚቢሽንና ባዛሩ "የኢትዮጵያ ምርት ለብልፅግና" በሚል መሪ ሀሳብ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሀምሌ 11/2017 ድረስ በአዲስ አበባ ኢግዚቪሽን ማዕከል ይካሄዳል። በመርሃ-ግብሩ መክፍቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ እና ሌሎችም ታድመዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኢግዚቢሽንና ባዛር በኢትዮጵያ የሚመረቱ ምርቶችና አገልግሎቶችን የመጠቀም ባህል ለማጎልበት ነው። የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ንቅናቄ የሀገሪቱን የንግድ ስርዓት ለማዘመን፣ ምርትና አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማጎልበት ያለመ መሆኑንም ተናግረዋል። የንግድ ሳምንቱ የአገር ውስጥ ምርቶችና አገልግሎቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥና በመግዛት በኩል ለማህበረሰብ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። የንግዱ ማህበረሰብም የንግድ ፍቃድ አውጥቶ በህጋዊ መንገድ በመስራት የዘርፉ ኢንቨስትመንት እንዲሻሻልና በዘመናዊ አሰራር እንዲካሄድ የራሱን እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባውም ነው የገለጹት። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው በከተማዋ የሚደረጉ የንግድ እንቅስቃሴዎች ለኢኮኖሚ እድገቱ ትልቅ ድርሻ እንደሚያበርክቱም ተናግረዋል።   ኢግዚቢሽንና ባዛሩ አምራቾችንና ሸማቾችን በቀጥታ በማገናኘት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገበያዩ ለማደረግ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ፤ ከተማ አስተዳደሩ የነዋሪውን የኑሮ ጫና ለማቃለል በከተማ ደረጃ ግብር ኃይል በማቋቋም እየሰራ ይገኛል ብለዋል።   በዚህም አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎቶች ለማህበረሰቡ እንዲደርሱ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በኢግዝብሽንና ባዛሩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት እንዳሉት ምርቶቻቸውን በዝግጅቱ ላይ በማቅረባቸው የተሻለ የንግድ ትስስር ለመፍጠር እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።     ምርቶቻቸውን ካቀረቡት መካከልም አቶ ኤልያስ አስቻለው፤ መንግስት መሰል ባዛሮችን ማዘጋጀቱ ለምርቶቻቸው ምቹ ገበያን ከመፍጠር ባሻገር በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል። ቀደም ብሎ በተካሄደው ኢግዚብሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ የገበያ ትስስርን በመፍጠር ምርቶቻቸውን በተሻለ መልኩ ለመሸጥ ምቹ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው የጠቀሱት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ትእግስት ተገኝ ናቸው ።
ግብርን በቴሌ ብር መክፈል ጊዜና እንግልትን ከማስቀረት ባለፈ ሀገራዊ ግዴታችንን በወቅቱ ለመወጣት እያገዘን ነው-በሲዳማ ክልል ግብር ከፋዮች
Jul 14, 2025 40
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦ ግብርን በቴሌ ብር መክፈል ጊዜያቸውን ከመቆጠብና እንግልትን ከማስቀረት ባለፈ ሀገራዊ ግዴታቸውን በወቅቱ ለመወጣት እያገዛቸው መሆኑን የሲዳማ ክልል ግብር ከፋዮች ገለጹ። የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን በበኩሉ በሰባት ቀናት ውስጥ በክልሉ ከሚገኙ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ አሰራር መዘርጋቱን አስታውቋል። በሲዳማ ክልል ከሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች በቴክኖሎጂ ታግዘው በቴሌ ብር ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ሲሆን ዘመናዊ አሰራሩ ጊዜንና እንግልትን ከመቀነስ ባለፈ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት እያገዛቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል በክልሉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ቦርጂ በማማከር አገልግሎት ከሚያገኙት ገቢ የሚጠበቅባቸውን ግብር በቴሌ ብር መክፈላቸው ጊዜያቸውን እንደቆጠበላቸው ገልጸዋል።   ግብርን በወቅቱ መክፈል መንግስት ለሚያከናውነው የልማት ሥራ አጋዥ መሆኑን ጠቁመው፣ የግብር አሰባሰቡ መዘመኑ ግብር ከፋዩ በወቅቱ የሚጠበቅበትን ለመወጣት እያስቻለው መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ ይርጋለም ከተማ የሚኖረት አቶ ምትኩ ጸጋዬ በበኩላቸው በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መዘርጋቱ ግብራቸውን በቴሌ ብር ለመክፈልና ጊዜያቸውን ለመቆጠብ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡   ግብር ለሃገር እድገት የሚኖረው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ምትኩ የሚጠበቅባቸውን ግብር በታማኝነት እንደከፈሉና ሌሎችም ሃላፊነታቸውን በወቅቱ መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታና ለልማት የሚደረግ አስተዋጽኦ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ የወንዶገነት ከተማ ነዋሪው አቶ ማሞ ቱላ ናቸው።   በሚኖሩበት ከተማ እየተከናወነ ያለው ፈጣን የልማት እንቅስቃሴ ግዴታቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረው፣ "አገልግሎቱ በቴሌ ብር መታገዙ ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ እንግልትን አስቀርቶልኛል" ብለዋል። የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተርና የደንበኞች አገልግሎት የታክስ አወሳሰንና የገቢ አሰባሰብ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ሙላት ዮሴፍ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በክልሉ ከ35ሺህ 816 በላይ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ ግብር ከፋዮችም በሰባት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር ተገብቷል ብለዋል።   በክልሉ ከሚገኙ 45 መዋቅሮች በ31ዱ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱ በቴሌብር ታግዞ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ ዘመናዊ የግብር አሰባሰብ ሥርአት መዘርጋቱ ለግብር ከፋዮች ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ከማስቻሉ ባለፈ ህገወጥ ተግባራትን ለመከላከል እያገዘ ነው ብለዋል። በተጨማሪም የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመዘርጋት ግብር ከፋዮች ንግድ ፈቃዳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሌሎች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን የሚያገኙበት አሰራር መዘርጋቱ እንግልት ያስቀረ፣ ጊዜና ጉልበት የቆጠበ ነው ሲሉም ምክትል ዳይሬክተሯ ገልጸዋል።  
የክረምቱ ዝናብ የሚፈጥረውን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀልበስ በትኩረት መስራት ይገባል-ኢንስቲትዩቱ
Jul 14, 2025 48
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦የክረምቱ ዝናብ የሚፈጥረውን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀልበስ በትኩረት መስራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ዝናቡ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የደቡብ ምዕራብ፣ምዕራብና ሰሜን ምዕራብ የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ዝናብ እንደሚኖር አመላክቷል። በምስራቅ፣ሰሜን ምስራቅ እና መካከለኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት እንደሚኖርም እንዲሁ። በሌላ በኩል በሰሜን ምስራቅ፤ መካከለኛው እና ምዕራብ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ አልፎ አልፎ ከሚጠናከሩ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በመነሳት ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር ጠቁሟል። የሚኖረው የዝናብ መጠን ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅሥቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንዳለው በማንሳት፤ የሚኖሩትን መልካም አጋጣሚዎች ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀነስ መስራት እንደሚገባም ገልጿል። በሚኖረው የአየር ሁኔታ በአብዛኛው ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖር ኢንስቲትዩቱ በትንበያው ጠቅሷል። አልፎ አልፎ ከሚኖር ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች፣ የከተማም ሆነ የገጠር አካባቢዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ፣ የወንዞች ከፍታ መጨመር ሊያስከትል እንደሚችልም አስጠንቅቋል። በመሆኑም የሚመለከታቸው የዘርፉ አካላት ሊኖር የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀትና የማፅዳት ስራ መስራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥቷል።
በሲዳማ ክልል እየተመዘገበ ላለው ለውጥ የክልሉ ምክር ቤት ሚናውን በመወጣት አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው-አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
Jul 14, 2025 54
ሀዋሳ ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል እየተመዘገበ ላለው ለውጥ የክልሉ ምክር ቤት ሚናውን በመወጣት ጉልህ አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው፡፡   የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ እንደገለጹት በክልሉ በልማትና በመልካም አስተዳደር ሥራዎች እየተመዘገቡ ባሉ ውጤቶች ላይ ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ አካላትን የሥራ አፈጻጸም ከመከታተል ባለፈ እስከ ታችኛው መዋቅሮች በመውረድ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች እየተከናወኑ ያሉበትን ሁኔታ እንደሚገመግም ተናግረዋል ፡፡ በተለይ የካፒታል ፕሮጀክቶች ያሉበትን ደረጃ የመገምገም እንዲሁም በአስፈፃሚ ተቋማት ላይ ድንገተኛ ክትትል የማድረግ ሥራ ምክር ቤቱ እንደሚያከናውን ጠቁመዋል። በዚህም ቀደም ሲል የካፒታል ፕሮጀክቶች ላይ ይታይ የነበረው የመጓተት ችግር እየተፈታ መምጣቱን አመልክተዋል። የፍትህ ስርዓቱን ለማጠናከር የሲዳማ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓት የሆነው "አፊኒ” በተደራጀ መንገድ እንዲመራ አዋጅና ሕጎችን በማውጣት ህብረተሰቡ ከመደበኛ የፍትሕ ሥርዐት በተጨማሪ እንዲጠቀምበት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። የዳኝነት ሥርዐቱን በተሻለ ዕውቀት እንዲመሩም ከ568 ቀበሌያት ለተውጣጡ የባህል መሪዎች ሥልጠና መሰጠቱንም አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።   በክልሉ በዓመት ለሁለት ጊዜ ህዝባዊ ፎረሞች እንደሚደረጉ የገለጹት ወይዘሮ ፋንታዬ፣ በእዚህም ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎች ለይቶ በመገምገም ለመፍትሄው እንዲሰራ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። ለአብነትም በዳራ ቀባዶ ሆስፒታል ተፈጥሮ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር ህዝባዊ የውይይት መድረክ በማዘጋጀት በተወሰደ እርምጃ ለማስተካከል መቻሉን ጠቅሰዋል። በኦዲት ግኝት 22 ሚሊዮን ብር የባከነ ገንዘብ ለማስመለስ እንደተቻለ ጠቁመው፣ 450 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ በአሰራር ብልሽት ይባክን የነበረ ገንዘብም ለማስተካከልና ለማዳን መቻሉን ተናግረዋል። በጉባኤው ያለፈው የምክርቤቱ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ የፀደቀ ሲሆን የምክር ቤቱ የበጀት ዓመቱ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትም ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው ፡፡    
የሚታይ
የሀገር ውስጥ ምርቶችን መጠቀምን ሁሉም ባህል ማድረግ አለበት - የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
Jul 14, 2025 51
  አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓትን በማሳለጥ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ባህልን ማጎልበት እንደሚገባ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) ገለጹ ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ያዘጋጀው 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛር ተከፍቷል።   ኤግዚቢሽንና ባዛሩ "የኢትዮጵያ ምርት ለብልፅግና" በሚል መሪ ሀሳብ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሀምሌ 11/2017 ድረስ በአዲስ አበባ ኢግዚቪሽን ማዕከል ይካሄዳል። በመርሃ-ግብሩ መክፍቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ እና ሌሎችም ታድመዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኢግዚቢሽንና ባዛር በኢትዮጵያ የሚመረቱ ምርቶችና አገልግሎቶችን የመጠቀም ባህል ለማጎልበት ነው። የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ንቅናቄ የሀገሪቱን የንግድ ስርዓት ለማዘመን፣ ምርትና አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማጎልበት ያለመ መሆኑንም ተናግረዋል። የንግድ ሳምንቱ የአገር ውስጥ ምርቶችና አገልግሎቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥና በመግዛት በኩል ለማህበረሰብ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። የንግዱ ማህበረሰብም የንግድ ፍቃድ አውጥቶ በህጋዊ መንገድ በመስራት የዘርፉ ኢንቨስትመንት እንዲሻሻልና በዘመናዊ አሰራር እንዲካሄድ የራሱን እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባውም ነው የገለጹት። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው በከተማዋ የሚደረጉ የንግድ እንቅስቃሴዎች ለኢኮኖሚ እድገቱ ትልቅ ድርሻ እንደሚያበርክቱም ተናግረዋል።   ኢግዚቢሽንና ባዛሩ አምራቾችንና ሸማቾችን በቀጥታ በማገናኘት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገበያዩ ለማደረግ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ፤ ከተማ አስተዳደሩ የነዋሪውን የኑሮ ጫና ለማቃለል በከተማ ደረጃ ግብር ኃይል በማቋቋም እየሰራ ይገኛል ብለዋል።   በዚህም አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎቶች ለማህበረሰቡ እንዲደርሱ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በኢግዝብሽንና ባዛሩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት እንዳሉት ምርቶቻቸውን በዝግጅቱ ላይ በማቅረባቸው የተሻለ የንግድ ትስስር ለመፍጠር እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።     ምርቶቻቸውን ካቀረቡት መካከልም አቶ ኤልያስ አስቻለው፤ መንግስት መሰል ባዛሮችን ማዘጋጀቱ ለምርቶቻቸው ምቹ ገበያን ከመፍጠር ባሻገር በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል። ቀደም ብሎ በተካሄደው ኢግዚብሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ የገበያ ትስስርን በመፍጠር ምርቶቻቸውን በተሻለ መልኩ ለመሸጥ ምቹ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው የጠቀሱት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ትእግስት ተገኝ ናቸው ።
የክረምቱ ዝናብ የሚፈጥረውን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀልበስ በትኩረት መስራት ይገባል-ኢንስቲትዩቱ
Jul 14, 2025 48
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦የክረምቱ ዝናብ የሚፈጥረውን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀልበስ በትኩረት መስራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ዝናቡ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የደቡብ ምዕራብ፣ምዕራብና ሰሜን ምዕራብ የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ዝናብ እንደሚኖር አመላክቷል። በምስራቅ፣ሰሜን ምስራቅ እና መካከለኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት እንደሚኖርም እንዲሁ። በሌላ በኩል በሰሜን ምስራቅ፤ መካከለኛው እና ምዕራብ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ አልፎ አልፎ ከሚጠናከሩ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በመነሳት ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር ጠቁሟል። የሚኖረው የዝናብ መጠን ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅሥቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንዳለው በማንሳት፤ የሚኖሩትን መልካም አጋጣሚዎች ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀነስ መስራት እንደሚገባም ገልጿል። በሚኖረው የአየር ሁኔታ በአብዛኛው ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖር ኢንስቲትዩቱ በትንበያው ጠቅሷል። አልፎ አልፎ ከሚኖር ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች፣ የከተማም ሆነ የገጠር አካባቢዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ፣ የወንዞች ከፍታ መጨመር ሊያስከትል እንደሚችልም አስጠንቅቋል። በመሆኑም የሚመለከታቸው የዘርፉ አካላት ሊኖር የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀትና የማፅዳት ስራ መስራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥቷል።
የጋራ ትርክትን በመገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታን ለመወሰን በሚደረገው ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ ነው-አቶ ዛዲግ አብርሃ
Jul 14, 2025 82
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦የጋራ ትርክትን በመገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታ ለመወሰን በሚደረገው ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ መሆኑን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለፁ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከአፍሪካ አመራር ልህቀት ማዕከል ጋር በመተባበር በትርክትና በአገር ግንባታ የጋዜጠኝነት ሚናን የተመለከተ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ለአራት ቀናት በሚቆየው ስልጠና የኢዜአ የማዕከልና ክልል ቅርንጫፍ ቢሮ ኃላፊዎችና ሰራተኞች እየተሳተፉ ይገኛሉ።   የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስለትርክት ምንነት፣ አስፈላጊነት፣ የትርክት ኃይልና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በስልጠናው ትርክት ማንነትን ለመቅረፅ፣ሰዎችን ለማነሳሳት፣ ባህልን ለማሻገር እንዲሁም ውሳኔ ለመወሰን የሚጠቅም መሆኑን አንስተዋል። ትርክት ዓለምን የምናይበት መነፅር መሆኑ ጠቅሰው፤ ትርክቷን የዘነጋች አገር እንዴት መነሳት እንዳለባት አታውቅም ብለዋል።   ትርክት ማንነትን የሚቀርፅ መሆኑና አገር የሚወለደው በጋራ ትርክት እንደሆነም አቶ ዛዲግ ገልፀዋል። የጋራ ትርክትን መገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታን ለመወሰን የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፤ ለጋራ ትርክት ግንባታ ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
ከተማ አስተዳደሩ የኩላሊት እጥበት ህክምና ተደራሽነትን ለማስፋት ከግሉ ዘርፍ ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 14, 2025 65
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦ከተማ አስተዳደሩ የኩላሊት እጥበት ህክምና ተደራሽነትን ለማስፋት ከግሉ ዘርፍ ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ለኩላሊት እጥበት ህክምና አገልግሎት የሚውሉ ቁሳቁሶችን ለዳግማዊ ምኒልክ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ድጋፍ አድርጓል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ከተማ አስተዳደሩ በሰው ተኮር ሥራዎቹ የኩላሊት እጥበት ህክምናን ለማስፋት እየሰራ ነው። ከተማ አስተዳደሩ በዘውዲቱ እና በዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታሎች የኩላሊት እጥበት ህክምና ወጪን በመሸፈን ታካሚዎች አገልግሎቱን በነጻ እንዲያገኙ ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል። በዚህም ከመላ ሀገሪቱ ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ታካሚዎችን እንግልት ለመቀነስ መስራቱን ጠቅሰው፥ አገልግሎቱን ለማስፋትም ዳያስፖራውን ጨምሮ በመንግሥትና በግል አጋርነት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ይህም በመክፈል አቅም ማነስ ምክንያት የኩላሊት እጥበት ለማድረግ የሚቸገሩ ዜጎች ህክምናውን እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቅሰዋል። ከችግሩ አሳሳቢነት አንፃር ከተማ አስተዳደሩ የህክምናውን ተደራሽነት ለማስፋት አሁንም ከግሉ ዘርፍ ጋር ያለውን ትብብር ማጠናከሩንም ገልጸዋል።   ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ያደረገው የኩላሊት ህክምና ማሽንና ሌሎች ቁሳቁሶች ድጋፍም የትብብር ስራው ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል።   የዛሬው ድጋፍ ታካሚዎቹ በሳምንት ሶስት ቀን የተሟላ የእጥበት ህክምና የሚያገኙበትን የማሽን እና የአልጋ ቁሳቁስ ያሟላ ነው ብለዋል ከንቲባዋ። ድርጅቱ ህይወት በሚያድኑ ተግባራት እያደረገ ላለው ድጋፍም በማመስገን፥ በቀጣይም አቅም የሌላቸውን ዜጎች እና ህሙማንን የመደገፍ የጋራ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሃንስ ጫላ በበኩላቸው፥ ከዚህ ቀደም በዘውዲቱ መታሰቢያ እና በዳግማዊ ምኒልክ አጠቃላይ ስፔላይዝድ ሆስፒታሎች በ20 የኩላሊት እጥበት ማሽኖች ለ144 ታካሚዎች አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር አውስተዋል።   የግብዓት ጉዳይ ፈታኝ ሆኖ መቆየቱን ያነሱት ኃላፊው፥ ዛሬ ከሜድሮክ የተረከቧቸው 20 የኩላሊት እጥበት ማሽን፣ 10 ዘመናዊ የታካሚዎች አልጋ እና ሌሎች የህክምና ግብዓቶች ፋይዳቸው የጎላ ነው ብለዋል። የዛሬው ድጋፍ የታካሚዎችን ቁጥር በእጥፍ የሚያሳድግ እና ለቀጣይ ሶስት ዓመታት ያልተቋረጠ የኩላሊት እጥበት ህክምናን መስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በመዲናዋ የኩላሊት እጥበት ህክምና አገልግሎትን ለማስፋት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል።   የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድ፥ ሜድሮክ ለአቅመ ደካሞች እያደረገ እና የህሙማንን ህይወትን የሚታደግ ስራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸው፥ በዚህም ተቋማዊ ክብር እና ደስታ ይሰማናል ብለዋል።   ድርጅቱ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በሲዳማ ክልል እየተመዘገበ ላለው ለውጥ የክልሉ ምክር ቤት ሚናውን በመወጣት አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው-አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
Jul 14, 2025 54
ሀዋሳ ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል እየተመዘገበ ላለው ለውጥ የክልሉ ምክር ቤት ሚናውን በመወጣት ጉልህ አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው፡፡   የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ እንደገለጹት በክልሉ በልማትና በመልካም አስተዳደር ሥራዎች እየተመዘገቡ ባሉ ውጤቶች ላይ ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ አካላትን የሥራ አፈጻጸም ከመከታተል ባለፈ እስከ ታችኛው መዋቅሮች በመውረድ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች እየተከናወኑ ያሉበትን ሁኔታ እንደሚገመግም ተናግረዋል ፡፡ በተለይ የካፒታል ፕሮጀክቶች ያሉበትን ደረጃ የመገምገም እንዲሁም በአስፈፃሚ ተቋማት ላይ ድንገተኛ ክትትል የማድረግ ሥራ ምክር ቤቱ እንደሚያከናውን ጠቁመዋል። በዚህም ቀደም ሲል የካፒታል ፕሮጀክቶች ላይ ይታይ የነበረው የመጓተት ችግር እየተፈታ መምጣቱን አመልክተዋል። የፍትህ ስርዓቱን ለማጠናከር የሲዳማ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓት የሆነው "አፊኒ” በተደራጀ መንገድ እንዲመራ አዋጅና ሕጎችን በማውጣት ህብረተሰቡ ከመደበኛ የፍትሕ ሥርዐት በተጨማሪ እንዲጠቀምበት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። የዳኝነት ሥርዐቱን በተሻለ ዕውቀት እንዲመሩም ከ568 ቀበሌያት ለተውጣጡ የባህል መሪዎች ሥልጠና መሰጠቱንም አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።   በክልሉ በዓመት ለሁለት ጊዜ ህዝባዊ ፎረሞች እንደሚደረጉ የገለጹት ወይዘሮ ፋንታዬ፣ በእዚህም ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎች ለይቶ በመገምገም ለመፍትሄው እንዲሰራ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። ለአብነትም በዳራ ቀባዶ ሆስፒታል ተፈጥሮ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር ህዝባዊ የውይይት መድረክ በማዘጋጀት በተወሰደ እርምጃ ለማስተካከል መቻሉን ጠቅሰዋል። በኦዲት ግኝት 22 ሚሊዮን ብር የባከነ ገንዘብ ለማስመለስ እንደተቻለ ጠቁመው፣ 450 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ በአሰራር ብልሽት ይባክን የነበረ ገንዘብም ለማስተካከልና ለማዳን መቻሉን ተናግረዋል። በጉባኤው ያለፈው የምክርቤቱ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ የፀደቀ ሲሆን የምክር ቤቱ የበጀት ዓመቱ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትም ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው ፡፡    
የጋራ ትርክትን በመገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታን ለመወሰን በሚደረገው ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ ነው-አቶ ዛዲግ አብርሃ
Jul 14, 2025 82
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦የጋራ ትርክትን በመገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታ ለመወሰን በሚደረገው ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ መሆኑን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለፁ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከአፍሪካ አመራር ልህቀት ማዕከል ጋር በመተባበር በትርክትና በአገር ግንባታ የጋዜጠኝነት ሚናን የተመለከተ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ለአራት ቀናት በሚቆየው ስልጠና የኢዜአ የማዕከልና ክልል ቅርንጫፍ ቢሮ ኃላፊዎችና ሰራተኞች እየተሳተፉ ይገኛሉ።   የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስለትርክት ምንነት፣ አስፈላጊነት፣ የትርክት ኃይልና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በስልጠናው ትርክት ማንነትን ለመቅረፅ፣ሰዎችን ለማነሳሳት፣ ባህልን ለማሻገር እንዲሁም ውሳኔ ለመወሰን የሚጠቅም መሆኑን አንስተዋል። ትርክት ዓለምን የምናይበት መነፅር መሆኑ ጠቅሰው፤ ትርክቷን የዘነጋች አገር እንዴት መነሳት እንዳለባት አታውቅም ብለዋል።   ትርክት ማንነትን የሚቀርፅ መሆኑና አገር የሚወለደው በጋራ ትርክት እንደሆነም አቶ ዛዲግ ገልፀዋል። የጋራ ትርክትን መገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታን ለመወሰን የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፤ ለጋራ ትርክት ግንባታ ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እየሰራች ነው
Jul 14, 2025 84
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አዳም ተስፋዬ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ለቀጣናው ሀገራት የተለያዩ ሥልጠናዎችን በማዘጋጀት ትብብርን ይበልጥ ለማጎልበት እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሶማሊያና ደቡብ ሱዳን ለመጡ ዲፕሎማቶች ለሶስት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።     የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አዳም ተስፋዬ በሥልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ በቀጣናው ትብብርን ይበልጥ ለማጎልበት እየሰራች ነው ብለዋል። ቀጣናው ሽብርተኝነት፣ ሕገወጥ ስደትና የጦር መሳሪያ ዝውውር እንዲሁም ሌሎች በተናጥል ሊፈቱ የማይችሉ ችግሮች ያሉበት መሆኑን አንስተዋል። ተግዳሮቶችን ለመፍታት ብዙ ጠቃሚ ተግባራት እየተከናወኑ ቢሆንም በቀጣይም ተጨማሪ እርምጃዎችን እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። ስልጠናው ችግሮችን ለመፍታት የጋራ ጥበቦችን እና ቁርጠኝነት የሚጠናከርበት አንዱ ጠቃሚ ተግባር መሆኑንም ገልጸዋል። የቀጣናውን ትብብር ማጠናከር እና በህዝቦች መካከል ጥልቅ መግባባት መፍጠር በስልጠናው መርሃ ግብር ከተቀመጡ ተልዕኮዎች መካከል መሆኑንም ተናግረዋል። በጋራ ክልላዊ ተግዳሮቶች ላይ የትብብር መድረክን መፍጠር፣ በአፍሪካ ቀንድ ገንቢ ተሳትፎን ማበረታታት እና ማሳደግ ሌላኛው ዓላማ እንደሆነ አክለዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የስልጠና ክፍል ዳይሬክተር ጀነራል መላኩ ሙሉዓለም በበኩላቸው፤ ስልጠናው በጋራ በሆኑ ቀጣናው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተናግረዋል።   ስልጠናው በፓን አፍሪካኒዝም፣ ድንበር ተሻጋሪ ሃብቶችን በጋራ መጠቀምና ሰላም ማስከበር ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። ከኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሶማሊያና ደቡብ ሱዳን የመጡ ዲፕሎማቶች እየተሳተፉ እንዳለ ጠቅሰዋል።
በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም መገንባት ትኩረት ተሰጥቷል
Jul 14, 2025 75
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም ማጎልበት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚና የኔዘርላንድስ መልቲ ፓርቲ ዴሞክራሲ ኢንስቲትዩት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የሦስትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል።     የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በመግባቢያ ስምምነቱ ሥነ-ሥርዓት ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለማዳበር በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አመራርና አባላትን አቅም መገንባት ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራር አባላትን አቅም ማጎልበት የሚያስችሉ ሥልጠናዎች ማዘጋጀት ወሳኝ ነው ብለዋል።   ምክር ቤቱ ከዚህ አኳያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋርም መስራቱ በዕወቀት የሚመራ አመራር ለመገንባት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዳበረ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ የልህቀት አካዳሚው ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል።   ለዚህ ደግሞ አካዳሚው በአገር በአቀል ዕውቀት የታገዘ የፖለቲካ ፓርቲዎች የስልጠና መመሪያና የአመራር ልማት ግንባታ እቅድና ስትራቴጂ ማዘጋጀቱንም ገልጸዋል። የኔዘርላንድ መልቲ ፓርቲ ዴሞክራሲ ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ተወካይ ይነበብ ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ጠንካራ የመድብለ-ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ የቴክኒክና የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል።   በመድብለ ፓርቲ ስርዓት ውስጥ እየተገነባ ላለው ዴሞክራሲ ስርዓት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፤ ከልህቀት አካዳሚው ጋርም በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በዛሬው ዕለት መፈራረማቸውን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ጠንካራ የመድበለ-ፓርቲ ሥርዓት በመገንባት ሂደት በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳትንት ዛዲግ አብረሃ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በዚህ ረገድ ተቋማቱ በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ-ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የተፈራረሙትን ስምምነት ውጤታማ ለማድረግ አቅማቸውን አሟጠው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
በዓመቱ የኢትዮጵያን የተረጂነት ታሪክ ለመቀየር መሰረት የጣሉ ሥራዎች ተከናውነዋል - አቶ አደም ፋራህ
Jul 14, 2025 82
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦በ2017 በጀት ዓመት ከተረጂነት ለመውጣት የተከናወኑ ሥራዎች የኢትዮጵያን የተረጂነት ታሪክ ለመቀየር መሰረት የጣሉ ናቸው አሉ የብልጽግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፡፡ የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲው ሥራዎች ማጠቃለያ የግምገማ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ አቶ አደም ፋራህ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር ፥ 2017 በጀት ዓመት በርካታ ሥራዎች የተከናወኑበት፣ የትጋት እና የስኬት ዓመት እንደነበር አንስተዋል፡፡ ፓርቲውን በሰብዓዊና በቁሳዊ ሃብት ለማጠናከር፣ በዘመናዊ መረጃ ለማደራጀት እንዲሁም ገዢ ትርክትና ቅቡልነትን ከማረጋገጥ አንጻር የተከናወኑ ሥራዎች ስኬታማ ናቸው ብለዋል። በአስተሳሰብ፣በአደረጃጀትና በአሰራር የተዋሃደ ፓርቲ ለመፍጠር የተሰሩ ሥራዎች ስኬታማ እንደነበሩ ጠቁመው፥ በዚህም የፓርቲውን 2ኛ መደበኛ ጉባዔና 5ኛ ዓመት ምስረታ በዓል በተቀናጀ መንገድ ማክበር ተችሏል ማለታቸውን የዘገበው ኤፍ ኤም ሲ ነው። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነትና ዘላቂነት ያለው እንዲሆን በትኩረት መሰራቱን የተናገሩት አቶ አደም፥ በዚህም አመርቂ ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል፡፡ በንቅናቄ የተከናወኑ ሥራዎች ውጤታማ እንደነበሩ እና ሕዝቡ አካታች ሀገራዊ ምክክር ላይ እንዲሳተፍ በመደረጉ የምክክር ሒደት በተሳካ መንገድ መቀጠሉን አስገንዝበዋል፡፡ ገዢ ትርክትና ቅቡልነት እንዲረጋገጥ በተከናወነው ሥራ ሀገራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ አዎንታዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ድሎችን ማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በመቅረፍ ለሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ ሕዝቡን በማሳተፍ መስራት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትን ለሌሎች ከተሞች ተሞክሮ በማካፈል ሁሉን አቀፍ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሰራ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 13, 2025 181
አሶሳ፤ሐምሌ 6/2017 (ኢዜአ)፦ከተማ አስተዳደሩ እያከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ለሌሎች ከተሞች ተሞክሮ በማካፈል ሁሉን አቀፍ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሰራ ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአመራር ለአመራር ግንኙነትና ልምድ ልውውጥ መድረክ ዛሬ በአሶሳ ከተማ ተካሄዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት፤ ከተማ አስተዳደሩ እያከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ለሌሎች ከተሞች ተሞክሮ በማካፈል ሁሉን አቀፍ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሰራ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት በአዲስ አበባ ከተማም በህብረተሰቡ ተሳትፎ እና በአመራሩ ቁርጠኝነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ተሞክሮን በማሳደግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉንም ከንቲባዋ ተናግረዋል። የሚከናወኑ የልማት ስራዎች ዘላቂ እና የረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው መሠራት እንዳለባቸውም ከንቲባዋ አስታውቀዋል። ​ በልማቱ ሂደት የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ህብረተሰቡ ለራሱ መሆኑን ማስገነዘብ እና የባለቤትነት ስሜት እንዲኖረው ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል። የአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት የሥራ እንቅስቃሴን የጎበኙት ከንቲባዋ፥ የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ የሚቀይር እና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርጋት መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የሚገኙ ባለሃብቶች በልማት ስራዎች ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ የቅርብ ግንኙነት በመፍጠር የልማት አሻራቸውን እንዲያሳርፉም በትብብር መሥራት ይጠበቃል ነው ያሉት። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአሶሳ ከተማ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ለማገዝ ዝግጁ መሆኑንም ከንቲባ አዳነች አቤቤ አረጋግጠዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አመራሮች በክልሉ የልማት ሥራዎች ላይ እያደረጉት ለሚገኘው ድጋፍ አመስግነዋል። ከከተማ አስተዳደሩ የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር የክልሉን የመሠረተ ልማት ተደራሽነት ለማሳደግ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ ይጀምራል
Jul 13, 2025 93
ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ እንደሚጀምር የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። ምክር ቤቱ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚያካሄደው ጉባኤ በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይም ተመልክቷል። የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ለኢዜአ እንዳሉት ምክር ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤውን ከነገ ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል። ምክር ቤቱ ከነገ ጀምሮ በሚያካሂደው 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውም በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ ተናግረዋል። ከአጀንዳዎቹ መካከልም የምክር ቤቱን የ8ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ የ2017 አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2018 ረቂቅ ዕቅድና በጀት ማፅደቅ እንደሚገኙበትም አፈ-ጉባኤዋ አመልክተዋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የኦዲት መስሪያ ቤቱ የ2017 ዓ/ም አፈጻጸም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድና በጀት ቀርቦ ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተገልጿል። እንዲሁም በምክር ቤቱ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና ሹመቶች ቀርበው እንደሚፀድቁም ዋና አፈ-ጉባኤዋ ተናግረዋል።  
ፖለቲካ
በሲዳማ ክልል እየተመዘገበ ላለው ለውጥ የክልሉ ምክር ቤት ሚናውን በመወጣት አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው-አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
Jul 14, 2025 54
ሀዋሳ ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል እየተመዘገበ ላለው ለውጥ የክልሉ ምክር ቤት ሚናውን በመወጣት ጉልህ አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው፡፡   የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ እንደገለጹት በክልሉ በልማትና በመልካም አስተዳደር ሥራዎች እየተመዘገቡ ባሉ ውጤቶች ላይ ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ አካላትን የሥራ አፈጻጸም ከመከታተል ባለፈ እስከ ታችኛው መዋቅሮች በመውረድ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች እየተከናወኑ ያሉበትን ሁኔታ እንደሚገመግም ተናግረዋል ፡፡ በተለይ የካፒታል ፕሮጀክቶች ያሉበትን ደረጃ የመገምገም እንዲሁም በአስፈፃሚ ተቋማት ላይ ድንገተኛ ክትትል የማድረግ ሥራ ምክር ቤቱ እንደሚያከናውን ጠቁመዋል። በዚህም ቀደም ሲል የካፒታል ፕሮጀክቶች ላይ ይታይ የነበረው የመጓተት ችግር እየተፈታ መምጣቱን አመልክተዋል። የፍትህ ስርዓቱን ለማጠናከር የሲዳማ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓት የሆነው "አፊኒ” በተደራጀ መንገድ እንዲመራ አዋጅና ሕጎችን በማውጣት ህብረተሰቡ ከመደበኛ የፍትሕ ሥርዐት በተጨማሪ እንዲጠቀምበት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። የዳኝነት ሥርዐቱን በተሻለ ዕውቀት እንዲመሩም ከ568 ቀበሌያት ለተውጣጡ የባህል መሪዎች ሥልጠና መሰጠቱንም አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።   በክልሉ በዓመት ለሁለት ጊዜ ህዝባዊ ፎረሞች እንደሚደረጉ የገለጹት ወይዘሮ ፋንታዬ፣ በእዚህም ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎች ለይቶ በመገምገም ለመፍትሄው እንዲሰራ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። ለአብነትም በዳራ ቀባዶ ሆስፒታል ተፈጥሮ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር ህዝባዊ የውይይት መድረክ በማዘጋጀት በተወሰደ እርምጃ ለማስተካከል መቻሉን ጠቅሰዋል። በኦዲት ግኝት 22 ሚሊዮን ብር የባከነ ገንዘብ ለማስመለስ እንደተቻለ ጠቁመው፣ 450 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ በአሰራር ብልሽት ይባክን የነበረ ገንዘብም ለማስተካከልና ለማዳን መቻሉን ተናግረዋል። በጉባኤው ያለፈው የምክርቤቱ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ የፀደቀ ሲሆን የምክር ቤቱ የበጀት ዓመቱ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትም ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው ፡፡    
የጋራ ትርክትን በመገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታን ለመወሰን በሚደረገው ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ ነው-አቶ ዛዲግ አብርሃ
Jul 14, 2025 82
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦የጋራ ትርክትን በመገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታ ለመወሰን በሚደረገው ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ መሆኑን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለፁ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከአፍሪካ አመራር ልህቀት ማዕከል ጋር በመተባበር በትርክትና በአገር ግንባታ የጋዜጠኝነት ሚናን የተመለከተ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ለአራት ቀናት በሚቆየው ስልጠና የኢዜአ የማዕከልና ክልል ቅርንጫፍ ቢሮ ኃላፊዎችና ሰራተኞች እየተሳተፉ ይገኛሉ።   የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስለትርክት ምንነት፣ አስፈላጊነት፣ የትርክት ኃይልና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በስልጠናው ትርክት ማንነትን ለመቅረፅ፣ሰዎችን ለማነሳሳት፣ ባህልን ለማሻገር እንዲሁም ውሳኔ ለመወሰን የሚጠቅም መሆኑን አንስተዋል። ትርክት ዓለምን የምናይበት መነፅር መሆኑ ጠቅሰው፤ ትርክቷን የዘነጋች አገር እንዴት መነሳት እንዳለባት አታውቅም ብለዋል።   ትርክት ማንነትን የሚቀርፅ መሆኑና አገር የሚወለደው በጋራ ትርክት እንደሆነም አቶ ዛዲግ ገልፀዋል። የጋራ ትርክትን መገንባት የጋራ መፃኢ እጣ ፈንታን ለመወሰን የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፤ ለጋራ ትርክት ግንባታ ሂደት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እየሰራች ነው
Jul 14, 2025 84
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አዳም ተስፋዬ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ለቀጣናው ሀገራት የተለያዩ ሥልጠናዎችን በማዘጋጀት ትብብርን ይበልጥ ለማጎልበት እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሶማሊያና ደቡብ ሱዳን ለመጡ ዲፕሎማቶች ለሶስት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።     የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አዳም ተስፋዬ በሥልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ በቀጣናው ትብብርን ይበልጥ ለማጎልበት እየሰራች ነው ብለዋል። ቀጣናው ሽብርተኝነት፣ ሕገወጥ ስደትና የጦር መሳሪያ ዝውውር እንዲሁም ሌሎች በተናጥል ሊፈቱ የማይችሉ ችግሮች ያሉበት መሆኑን አንስተዋል። ተግዳሮቶችን ለመፍታት ብዙ ጠቃሚ ተግባራት እየተከናወኑ ቢሆንም በቀጣይም ተጨማሪ እርምጃዎችን እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። ስልጠናው ችግሮችን ለመፍታት የጋራ ጥበቦችን እና ቁርጠኝነት የሚጠናከርበት አንዱ ጠቃሚ ተግባር መሆኑንም ገልጸዋል። የቀጣናውን ትብብር ማጠናከር እና በህዝቦች መካከል ጥልቅ መግባባት መፍጠር በስልጠናው መርሃ ግብር ከተቀመጡ ተልዕኮዎች መካከል መሆኑንም ተናግረዋል። በጋራ ክልላዊ ተግዳሮቶች ላይ የትብብር መድረክን መፍጠር፣ በአፍሪካ ቀንድ ገንቢ ተሳትፎን ማበረታታት እና ማሳደግ ሌላኛው ዓላማ እንደሆነ አክለዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የስልጠና ክፍል ዳይሬክተር ጀነራል መላኩ ሙሉዓለም በበኩላቸው፤ ስልጠናው በጋራ በሆኑ ቀጣናው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተናግረዋል።   ስልጠናው በፓን አፍሪካኒዝም፣ ድንበር ተሻጋሪ ሃብቶችን በጋራ መጠቀምና ሰላም ማስከበር ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። ከኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሶማሊያና ደቡብ ሱዳን የመጡ ዲፕሎማቶች እየተሳተፉ እንዳለ ጠቅሰዋል።
በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም መገንባት ትኩረት ተሰጥቷል
Jul 14, 2025 75
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም ማጎልበት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚና የኔዘርላንድስ መልቲ ፓርቲ ዴሞክራሲ ኢንስቲትዩት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የሦስትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል።     የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በመግባቢያ ስምምነቱ ሥነ-ሥርዓት ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለማዳበር በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አመራርና አባላትን አቅም መገንባት ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራር አባላትን አቅም ማጎልበት የሚያስችሉ ሥልጠናዎች ማዘጋጀት ወሳኝ ነው ብለዋል።   ምክር ቤቱ ከዚህ አኳያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋርም መስራቱ በዕወቀት የሚመራ አመራር ለመገንባት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዳበረ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ የልህቀት አካዳሚው ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል።   ለዚህ ደግሞ አካዳሚው በአገር በአቀል ዕውቀት የታገዘ የፖለቲካ ፓርቲዎች የስልጠና መመሪያና የአመራር ልማት ግንባታ እቅድና ስትራቴጂ ማዘጋጀቱንም ገልጸዋል። የኔዘርላንድ መልቲ ፓርቲ ዴሞክራሲ ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ተወካይ ይነበብ ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ጠንካራ የመድብለ-ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ የቴክኒክና የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል።   በመድብለ ፓርቲ ስርዓት ውስጥ እየተገነባ ላለው ዴሞክራሲ ስርዓት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፤ ከልህቀት አካዳሚው ጋርም በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በዛሬው ዕለት መፈራረማቸውን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ጠንካራ የመድበለ-ፓርቲ ሥርዓት በመገንባት ሂደት በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳትንት ዛዲግ አብረሃ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በዚህ ረገድ ተቋማቱ በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ-ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የተፈራረሙትን ስምምነት ውጤታማ ለማድረግ አቅማቸውን አሟጠው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
በዓመቱ የኢትዮጵያን የተረጂነት ታሪክ ለመቀየር መሰረት የጣሉ ሥራዎች ተከናውነዋል - አቶ አደም ፋራህ
Jul 14, 2025 82
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦በ2017 በጀት ዓመት ከተረጂነት ለመውጣት የተከናወኑ ሥራዎች የኢትዮጵያን የተረጂነት ታሪክ ለመቀየር መሰረት የጣሉ ናቸው አሉ የብልጽግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፡፡ የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲው ሥራዎች ማጠቃለያ የግምገማ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ አቶ አደም ፋራህ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር ፥ 2017 በጀት ዓመት በርካታ ሥራዎች የተከናወኑበት፣ የትጋት እና የስኬት ዓመት እንደነበር አንስተዋል፡፡ ፓርቲውን በሰብዓዊና በቁሳዊ ሃብት ለማጠናከር፣ በዘመናዊ መረጃ ለማደራጀት እንዲሁም ገዢ ትርክትና ቅቡልነትን ከማረጋገጥ አንጻር የተከናወኑ ሥራዎች ስኬታማ ናቸው ብለዋል። በአስተሳሰብ፣በአደረጃጀትና በአሰራር የተዋሃደ ፓርቲ ለመፍጠር የተሰሩ ሥራዎች ስኬታማ እንደነበሩ ጠቁመው፥ በዚህም የፓርቲውን 2ኛ መደበኛ ጉባዔና 5ኛ ዓመት ምስረታ በዓል በተቀናጀ መንገድ ማክበር ተችሏል ማለታቸውን የዘገበው ኤፍ ኤም ሲ ነው። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነትና ዘላቂነት ያለው እንዲሆን በትኩረት መሰራቱን የተናገሩት አቶ አደም፥ በዚህም አመርቂ ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል፡፡ በንቅናቄ የተከናወኑ ሥራዎች ውጤታማ እንደነበሩ እና ሕዝቡ አካታች ሀገራዊ ምክክር ላይ እንዲሳተፍ በመደረጉ የምክክር ሒደት በተሳካ መንገድ መቀጠሉን አስገንዝበዋል፡፡ ገዢ ትርክትና ቅቡልነት እንዲረጋገጥ በተከናወነው ሥራ ሀገራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ አዎንታዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ድሎችን ማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በመቅረፍ ለሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ ሕዝቡን በማሳተፍ መስራት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትን ለሌሎች ከተሞች ተሞክሮ በማካፈል ሁሉን አቀፍ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሰራ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 13, 2025 181
አሶሳ፤ሐምሌ 6/2017 (ኢዜአ)፦ከተማ አስተዳደሩ እያከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ለሌሎች ከተሞች ተሞክሮ በማካፈል ሁሉን አቀፍ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሰራ ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአመራር ለአመራር ግንኙነትና ልምድ ልውውጥ መድረክ ዛሬ በአሶሳ ከተማ ተካሄዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት፤ ከተማ አስተዳደሩ እያከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ለሌሎች ከተሞች ተሞክሮ በማካፈል ሁሉን አቀፍ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሰራ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት በአዲስ አበባ ከተማም በህብረተሰቡ ተሳትፎ እና በአመራሩ ቁርጠኝነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ተሞክሮን በማሳደግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉንም ከንቲባዋ ተናግረዋል። የሚከናወኑ የልማት ስራዎች ዘላቂ እና የረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው መሠራት እንዳለባቸውም ከንቲባዋ አስታውቀዋል። ​ በልማቱ ሂደት የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ህብረተሰቡ ለራሱ መሆኑን ማስገነዘብ እና የባለቤትነት ስሜት እንዲኖረው ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል። የአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት የሥራ እንቅስቃሴን የጎበኙት ከንቲባዋ፥ የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ የሚቀይር እና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርጋት መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የሚገኙ ባለሃብቶች በልማት ስራዎች ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ የቅርብ ግንኙነት በመፍጠር የልማት አሻራቸውን እንዲያሳርፉም በትብብር መሥራት ይጠበቃል ነው ያሉት። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአሶሳ ከተማ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ለማገዝ ዝግጁ መሆኑንም ከንቲባ አዳነች አቤቤ አረጋግጠዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አመራሮች በክልሉ የልማት ሥራዎች ላይ እያደረጉት ለሚገኘው ድጋፍ አመስግነዋል። ከከተማ አስተዳደሩ የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር የክልሉን የመሠረተ ልማት ተደራሽነት ለማሳደግ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ ይጀምራል
Jul 13, 2025 93
ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ማካሄድ እንደሚጀምር የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። ምክር ቤቱ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚያካሄደው ጉባኤ በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይም ተመልክቷል። የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ ለኢዜአ እንዳሉት ምክር ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤውን ከነገ ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል። ምክር ቤቱ ከነገ ጀምሮ በሚያካሂደው 6ኛ ምርጫ ዘመን 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውም በ11 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ ተናግረዋል። ከአጀንዳዎቹ መካከልም የምክር ቤቱን የ8ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ የ2017 አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2018 ረቂቅ ዕቅድና በጀት ማፅደቅ እንደሚገኙበትም አፈ-ጉባኤዋ አመልክተዋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የኦዲት መስሪያ ቤቱ የ2017 ዓ/ም አፈጻጸም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድና በጀት ቀርቦ ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተገልጿል። እንዲሁም በምክር ቤቱ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና ሹመቶች ቀርበው እንደሚፀድቁም ዋና አፈ-ጉባኤዋ ተናግረዋል።  
ማህበራዊ
ከተማ አስተዳደሩ የኩላሊት እጥበት ህክምና ተደራሽነትን ለማስፋት ከግሉ ዘርፍ ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 14, 2025 65
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦ከተማ አስተዳደሩ የኩላሊት እጥበት ህክምና ተደራሽነትን ለማስፋት ከግሉ ዘርፍ ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ለኩላሊት እጥበት ህክምና አገልግሎት የሚውሉ ቁሳቁሶችን ለዳግማዊ ምኒልክ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ድጋፍ አድርጓል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ከተማ አስተዳደሩ በሰው ተኮር ሥራዎቹ የኩላሊት እጥበት ህክምናን ለማስፋት እየሰራ ነው። ከተማ አስተዳደሩ በዘውዲቱ እና በዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታሎች የኩላሊት እጥበት ህክምና ወጪን በመሸፈን ታካሚዎች አገልግሎቱን በነጻ እንዲያገኙ ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል። በዚህም ከመላ ሀገሪቱ ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ታካሚዎችን እንግልት ለመቀነስ መስራቱን ጠቅሰው፥ አገልግሎቱን ለማስፋትም ዳያስፖራውን ጨምሮ በመንግሥትና በግል አጋርነት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ይህም በመክፈል አቅም ማነስ ምክንያት የኩላሊት እጥበት ለማድረግ የሚቸገሩ ዜጎች ህክምናውን እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቅሰዋል። ከችግሩ አሳሳቢነት አንፃር ከተማ አስተዳደሩ የህክምናውን ተደራሽነት ለማስፋት አሁንም ከግሉ ዘርፍ ጋር ያለውን ትብብር ማጠናከሩንም ገልጸዋል።   ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ያደረገው የኩላሊት ህክምና ማሽንና ሌሎች ቁሳቁሶች ድጋፍም የትብብር ስራው ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል።   የዛሬው ድጋፍ ታካሚዎቹ በሳምንት ሶስት ቀን የተሟላ የእጥበት ህክምና የሚያገኙበትን የማሽን እና የአልጋ ቁሳቁስ ያሟላ ነው ብለዋል ከንቲባዋ። ድርጅቱ ህይወት በሚያድኑ ተግባራት እያደረገ ላለው ድጋፍም በማመስገን፥ በቀጣይም አቅም የሌላቸውን ዜጎች እና ህሙማንን የመደገፍ የጋራ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሃንስ ጫላ በበኩላቸው፥ ከዚህ ቀደም በዘውዲቱ መታሰቢያ እና በዳግማዊ ምኒልክ አጠቃላይ ስፔላይዝድ ሆስፒታሎች በ20 የኩላሊት እጥበት ማሽኖች ለ144 ታካሚዎች አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር አውስተዋል።   የግብዓት ጉዳይ ፈታኝ ሆኖ መቆየቱን ያነሱት ኃላፊው፥ ዛሬ ከሜድሮክ የተረከቧቸው 20 የኩላሊት እጥበት ማሽን፣ 10 ዘመናዊ የታካሚዎች አልጋ እና ሌሎች የህክምና ግብዓቶች ፋይዳቸው የጎላ ነው ብለዋል። የዛሬው ድጋፍ የታካሚዎችን ቁጥር በእጥፍ የሚያሳድግ እና ለቀጣይ ሶስት ዓመታት ያልተቋረጠ የኩላሊት እጥበት ህክምናን መስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በመዲናዋ የኩላሊት እጥበት ህክምና አገልግሎትን ለማስፋት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል።   የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድ፥ ሜድሮክ ለአቅመ ደካሞች እያደረገ እና የህሙማንን ህይወትን የሚታደግ ስራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸው፥ በዚህም ተቋማዊ ክብር እና ደስታ ይሰማናል ብለዋል።   ድርጅቱ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በክልሉ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል እና የተማሪዎች ምገባ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jul 14, 2025 55
ባሕርዳር፤ ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የመምህራን አቅም ግንባታ ፣ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል እና የተማሪዎች ምገባ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ። ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የቀጣይ አምስት አመት ስትራቴጅክ ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እያካሄደ ነው።   በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት፤ ያለፈው የትምህርት ዘመን ክፍተቶችን በቀጣዩ ዘመን ለማካካስ የሚያስችል ዕቅድ ተይዞ ከወዲሁ እየተሰራ ነው። የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ አዲሱን የትምህርት ስርዓት ታሳቢ ያደረገ የመምህራን አቅም ግንባታ ፣የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል እና የተማሪዎች ምገባ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በአዲሱ በጀት ዓመት ከዚህ ቀደም ያቋረጡትንና ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናትን በመመዝገብ ያለፉትን ዓመታት ሊያካክስ የሚችል ስራ እንደሚከናወን ተናግረዋል። ስለትምህርት የማያገባው የሕብረተሰብ ክፍል እንደሌለ ያመለከቱት ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) ፤ ለዕቅዱ መሳካት ሁሉም አካል ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። በ2018 የትምህርት ዘመን ከሰባት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን መዝግቦ ለማስተማር ታቅዶ ከወዲሁ ዝግጀት እየተደረገ መሆኑም ተመልክቷል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው መድረክ የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች እየተሳተፉ ነው።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሪፎርም ስራዎቹ ኢትዮጵያን የሚመጥን ዘመናዊ አሰራር ገንብቷል
Jul 14, 2025 142
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፦ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባከናወናቸው የሪፎርም ስራዎች ኢትዮጵያን የሚመጥን ዘመናዊ አሰራር መገንባቱን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከክልል መዝጋቢ እና ባለድርሻ አካላት ጋር የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ያተኮረ ጉባኤ እያካሄደ ነው።   በመድረኩ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት፣ የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ጠይባ ሀሰን፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራር እና አባላት እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ታድመዋል። ዋና ዳይሬክተሯ ሰላማዊት ዳዊት በመክፈቻ ንግግራቸው፥ አገልግሎቱ ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በርካታ ችግሮች እንደነበሩበት አስታውሰዋል። ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን ከማሟላት አንጻርም ጉድለቶች እንደነበሩ በመጥቀስ፥ አገልግሎቶቹ ከማህበረሰቡ ፍላጎት ጋር ያልተጣጣሙ ሆነው መቆየታቸውን አንስተዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ፈጣንና ሁሉን አቀፍ ሪፎርም በማድረግ የብልጽግና ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ጠቅሰው አገልግሎቱም ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ሪፎርም ማካሄዱን ገልጸዋል። ለዚህም 11 የሪፎርም አጀንዳዎች ተቀርጸው ወደ ስራ መገባቱን በማውሳት፥ ኋላቀር የነበረውን የባዮሜትሪክ መረጃ መቀበያ ስርዓት ወደ ዘመናዊ አሰራር መቀየር መቻሉን ተናግረዋል። በዚህም የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት በማተም ችግሩን በጉልህ መቅረፍ መቻሉን ተናግረው ከአስር በላይ የጉዞ ሰነዶች እንዲዘምኑ መደረጋቸውን አስረድተዋል። የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን ወደ ዲጂታላይዜሽን ስኬታማ ሽግግር መደረጉን ገልጸው፥ በተቋሙ የሪፎርም ሥራዎች ኢትዮጵያን የሚመጥን ዘመናዊ አሰራር ገንብተናል ነው ያሉት። ከዜጎች ፍላጎት አንጻር በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎቱን ይበልጥ በማዘመንና በማቀላጠፍ የህዝብ እርካታን ለማሳደግ ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል። ባለድርሻ አካላትም ለአገልግሎቱ ግብ መሳካት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።  
ኢኮኖሚ
የሀገር ውስጥ ምርቶችን መጠቀምን ሁሉም ባህል ማድረግ አለበት - የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
Jul 14, 2025 51
  አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓትን በማሳለጥ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ባህልን ማጎልበት እንደሚገባ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) ገለጹ ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ያዘጋጀው 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛር ተከፍቷል።   ኤግዚቢሽንና ባዛሩ "የኢትዮጵያ ምርት ለብልፅግና" በሚል መሪ ሀሳብ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሀምሌ 11/2017 ድረስ በአዲስ አበባ ኢግዚቪሽን ማዕከል ይካሄዳል። በመርሃ-ግብሩ መክፍቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ እና ሌሎችም ታድመዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኢግዚቢሽንና ባዛር በኢትዮጵያ የሚመረቱ ምርቶችና አገልግሎቶችን የመጠቀም ባህል ለማጎልበት ነው። የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ንቅናቄ የሀገሪቱን የንግድ ስርዓት ለማዘመን፣ ምርትና አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማጎልበት ያለመ መሆኑንም ተናግረዋል። የንግድ ሳምንቱ የአገር ውስጥ ምርቶችና አገልግሎቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥና በመግዛት በኩል ለማህበረሰብ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። የንግዱ ማህበረሰብም የንግድ ፍቃድ አውጥቶ በህጋዊ መንገድ በመስራት የዘርፉ ኢንቨስትመንት እንዲሻሻልና በዘመናዊ አሰራር እንዲካሄድ የራሱን እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባውም ነው የገለጹት። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው በከተማዋ የሚደረጉ የንግድ እንቅስቃሴዎች ለኢኮኖሚ እድገቱ ትልቅ ድርሻ እንደሚያበርክቱም ተናግረዋል።   ኢግዚቢሽንና ባዛሩ አምራቾችንና ሸማቾችን በቀጥታ በማገናኘት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገበያዩ ለማደረግ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ፤ ከተማ አስተዳደሩ የነዋሪውን የኑሮ ጫና ለማቃለል በከተማ ደረጃ ግብር ኃይል በማቋቋም እየሰራ ይገኛል ብለዋል።   በዚህም አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎቶች ለማህበረሰቡ እንዲደርሱ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በኢግዝብሽንና ባዛሩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት እንዳሉት ምርቶቻቸውን በዝግጅቱ ላይ በማቅረባቸው የተሻለ የንግድ ትስስር ለመፍጠር እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።     ምርቶቻቸውን ካቀረቡት መካከልም አቶ ኤልያስ አስቻለው፤ መንግስት መሰል ባዛሮችን ማዘጋጀቱ ለምርቶቻቸው ምቹ ገበያን ከመፍጠር ባሻገር በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል። ቀደም ብሎ በተካሄደው ኢግዚብሽንና ባዛር ላይ በመሳተፍ የገበያ ትስስርን በመፍጠር ምርቶቻቸውን በተሻለ መልኩ ለመሸጥ ምቹ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው የጠቀሱት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ትእግስት ተገኝ ናቸው ።
ግብርን በቴሌ ብር መክፈል ጊዜና እንግልትን ከማስቀረት ባለፈ ሀገራዊ ግዴታችንን በወቅቱ ለመወጣት እያገዘን ነው-በሲዳማ ክልል ግብር ከፋዮች
Jul 14, 2025 40
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦ ግብርን በቴሌ ብር መክፈል ጊዜያቸውን ከመቆጠብና እንግልትን ከማስቀረት ባለፈ ሀገራዊ ግዴታቸውን በወቅቱ ለመወጣት እያገዛቸው መሆኑን የሲዳማ ክልል ግብር ከፋዮች ገለጹ። የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን በበኩሉ በሰባት ቀናት ውስጥ በክልሉ ከሚገኙ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ አሰራር መዘርጋቱን አስታውቋል። በሲዳማ ክልል ከሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች በቴክኖሎጂ ታግዘው በቴሌ ብር ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ሲሆን ዘመናዊ አሰራሩ ጊዜንና እንግልትን ከመቀነስ ባለፈ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት እያገዛቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል በክልሉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ቦርጂ በማማከር አገልግሎት ከሚያገኙት ገቢ የሚጠበቅባቸውን ግብር በቴሌ ብር መክፈላቸው ጊዜያቸውን እንደቆጠበላቸው ገልጸዋል።   ግብርን በወቅቱ መክፈል መንግስት ለሚያከናውነው የልማት ሥራ አጋዥ መሆኑን ጠቁመው፣ የግብር አሰባሰቡ መዘመኑ ግብር ከፋዩ በወቅቱ የሚጠበቅበትን ለመወጣት እያስቻለው መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ ይርጋለም ከተማ የሚኖረት አቶ ምትኩ ጸጋዬ በበኩላቸው በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መዘርጋቱ ግብራቸውን በቴሌ ብር ለመክፈልና ጊዜያቸውን ለመቆጠብ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡   ግብር ለሃገር እድገት የሚኖረው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ምትኩ የሚጠበቅባቸውን ግብር በታማኝነት እንደከፈሉና ሌሎችም ሃላፊነታቸውን በወቅቱ መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታና ለልማት የሚደረግ አስተዋጽኦ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ የወንዶገነት ከተማ ነዋሪው አቶ ማሞ ቱላ ናቸው።   በሚኖሩበት ከተማ እየተከናወነ ያለው ፈጣን የልማት እንቅስቃሴ ግዴታቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረው፣ "አገልግሎቱ በቴሌ ብር መታገዙ ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ እንግልትን አስቀርቶልኛል" ብለዋል። የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተርና የደንበኞች አገልግሎት የታክስ አወሳሰንና የገቢ አሰባሰብ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ሙላት ዮሴፍ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በክልሉ ከ35ሺህ 816 በላይ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ ግብር ከፋዮችም በሰባት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር ተገብቷል ብለዋል።   በክልሉ ከሚገኙ 45 መዋቅሮች በ31ዱ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱ በቴሌብር ታግዞ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ ዘመናዊ የግብር አሰባሰብ ሥርአት መዘርጋቱ ለግብር ከፋዮች ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ከማስቻሉ ባለፈ ህገወጥ ተግባራትን ለመከላከል እያገዘ ነው ብለዋል። በተጨማሪም የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመዘርጋት ግብር ከፋዮች ንግድ ፈቃዳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሌሎች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን የሚያገኙበት አሰራር መዘርጋቱ እንግልት ያስቀረ፣ ጊዜና ጉልበት የቆጠበ ነው ሲሉም ምክትል ዳይሬክተሯ ገልጸዋል።  
አፍሪ ኤግዚም ባንክ የአፍሪካን የልማት እና ትስስር ፕሮጀክቶች መደገፉን ይቀጥላል
Jul 14, 2025 68
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ኤክስፖርት እና ኢምፖርት ባንክ(አፍሪ ኤግዚም ባንክ) ለአፍሪካን የልማት እና ትስስር ፕሮጀክቶች የሚያደርገውን ድጋፍ በተጠናከረ መልኩ መደገፉን እንደሚቀጥል አስታወቀ። 47ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እና 7ኛው የህብረቱ ቀጣናዊ ማህበረሰቦች የመንፈቅ ዓመት የጋራ የትብብር ስብሰባ በኢኳቶሪያል ጊኒ ማላቦ ተካሂዷል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከተሰናባቹ የአፍሪካ ኤክስፖርት እና ኢምፖርት ባንክ(አፍሪ ኤግዚም ባንክ) ተሰናባች ፕሬዝዳንት እና የቦርድ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር ቤኔዲክት ኦርማህ ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱ የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪ ኤግዚም ባንክ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጎልበትና ባንኩ ለአፍሪካ ልማት እና ትስስር የሚያደርገውን ድጋፍ የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ ባንኩ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን መከላከልን ጨምሮ ለአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራትና ለኮሚሽኑ እያደረገ ያለውን ዘላቂ ድጋፍ አድንቀዋል።   በተጨማሪም ሊቀ መንበሩ ከአዲሱ የባንኩ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ኢሎምቢ(ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ማረጋገጣቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በዞኑ የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች ምርትና አገልግሎታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው
Jul 14, 2025 65
ነገሌ ቦረና፤ ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ቦረና ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች ምርትና አገልግሎታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ ተገለጸ። በዞኑ የስራ እድል ፈጠና ክህሎት ጽህፈት ቤት የስራ እድል ፈጠራ ቡድን መሪ አቶ ጎዳና ሳራ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በዞኑ ለ42ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መመቻቸቱን ለኢዜአ ተናግረዋል።   ከእነዚህም መካከል ከ10ሺህ 560 በላይ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ሰልጥነው የተመረቁ ናቸው ብለዋል፡፡ ነገሌ ቦረና ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ አጠቃላይ በዞኑ ወደ ስራ ከገቡት ወጣቶች መካከል 15ሺህ 971 ሴቶች እንደሆኑም አንስተዋል፡፡ ወጣቶቹ ወደ ስራ የገቡት በግብርና፣ በአገልግሎትና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ሲሆን፤ ግንባታ፣ ንግድ፣ እንስሳት እርባታ፣ ማዕድን ፍለጋና ግብይት፤ የቤትና የቢሮ እቃዎች ማመርተ ሰፊውን ድርሻ ይወስዳሉ ብለዋል። ወደ ስራ ለገቡት ወጣቶች 78 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ብድር በማመቻቸት ትራክተር፣ ከ10 ሄክታር በላይ የማምረቻ እና መሸጫ ቦታና 61 የመሸጫ ሱቆች ድጋፍ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡   ወደ ስራ የገቡ ወጣቶችም ምርትና አገልግሎታቸውን በብዛትና በጥራት ለገበያ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ የነገሌ ቦረና ከተማ ነዋሪ አልዬ ዋቆ ከ3 ባልደረቦቹ ጋር በልብስ ስፌትና የአልባሳት ምርት አቅርቦት ስራ ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል አንዱ ሲሆን፤ አልባሳቱ ባህልን ከማስተዋወቅ ባለፈ በገበያ አዋጭ በመሆኑ የተሻለ ገቢ የሚያስገኝ ተመራጭ የስራ ዘርፍ መሆኑን ገልጿል፡፡ በውጤቱም እራሳችንንና ቤተሰቦቻችንን ከመርዳት አልፈን ከንግድ ስራው የምናገኘውን ትርፍ መቆጠብ ጀምረናል ሲልም ተናግሯል፡፡ ሌላው የከተማው ነዋሪ ወጣት ቢኒያም አምሳሉና 2 ባልደረቦቹ በብረታ ብረት የስራ ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው። ወጣት ቢኒያም በሰጠው አስተያየት፤ ምርታችንን በጥራት እያመረትን ለነገሌ ቦረና ከተማ ህዝብና ለሴክተር መስሪያ ቤቶች ጭምር እያቀረብን ነው ብሏል። አሁን ላይ ካፒታላቸው 150ሺህ ብር መድረሱን ገልጸው በቀጣይም ስራቸውን ለማስፋፋት ተጨማሪ ብድር ለመውሰድ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በሀገር ደረጃ የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ተደራሽ እየተደረጉ ነው - የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት
Jul 13, 2025 119
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በሀገር ደረጃ የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ጸጋ ገለጹ። ባለፉት የለውጥ አመታት 280 የሚሆኑ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ጸጋ ኢንስቲትዩቱ በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ጥናት የሚያደርግ ተቋም ነው ብለዋል። በዚህም 52 የትኩረት መስኮችን በመለየት በ14 ዲፓርትመንቶች 6 ማእከሎችን በማዘጋጀት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የምርምር ስራዎቹም በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን አመላክተዋል። ማስረጃን መሰረት ያደረጉ የጥናት ውጤቶችንም ለሚመለከታቸው ፖሊሲ አውጪዎች እና አስፈጻሚዎች ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት 280 የሚሆኑ ምርምሮች መደረጋቸውን ተናግረዋል። እነዚህ ምርምሮችም ነባር ፖሊሲዎችን የፈተሹ፣ አዳዲስ ፖሊሲዎችን ያመላከቱ እና ፋይዳ ምልከታ ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የጥናት መነሻዎቹ እንደ ሀገር የተቀመጡ እቅዶች እና የመንግስት አቅጣጫዎች መሆናቸውን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ፈጣን እደገት ያስመዘገቡ ሀገራት ትልልቅ የምርምር ተቋማት እንዳላቸው አንስተዋል። እንደ ሀገር የተቀመጡ ግቦች እና ህልሞች እውን እንዲሆኑ በጥናት መደገፍ እንደሚገባ በመግለጽ። ኢንስቲትዩቱ በዚህ ረገድ የተሰጠውን ተልእኮ በመውሰድ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ጥናቶችን በማጥናት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በተለዩ የትኩረት መስኮች ላይ ፖሊሲዎች ከመነደፋቸው በፊት የምርምር ስራዎች እንደሚሰሩ አንስተው፤ ተፈጻሚ ከሆኑ በኋላም ምን አይነት ውጤት አመጣ የሚለው እየተሰራበት መሆኑን ገልጸዋል። ለአንድ ሀገር እድገት ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶች አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ኢንስቲትዩቱም እንደ ሀገር የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶችን ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አመላክተዋል። በዚህ አመትም በኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ 35 ጥናቶች መጠናታቸውን ተናግረዋል።  
ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከ19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች ተመዝግበዋል
Jul 13, 2025 99
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እስካሁን ከ19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች መመዝገባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ገለጹ። በኢትዮጵያ የነዋሪዎችን የመታወቅ መብት ለማረጋገጥ፣ በአገልግሎት ሰጭና ተቀባዮች መካከል መተማመን እንዲዳብር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና የተሳለጠ አሰራር ለመዘርጋት የዲጂታል መታወቂያ ገቢራዊ ተደርጓል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት በአዲስ አበባ እና በክልል የዲጂታል የመታወቂያ ምዝገባ ማከናወንና ከተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ፡፡ ይህንን ተከትሎ እስካሁን 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን ነዋሪዎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውንና ከ55 ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል ፡፡   በ2018 በጀት አመት የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን የበለጠ ለማሳደግ እቅድ መያዙንና ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡ በተለይ በክልሎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን ይበልጥ ለማስፋት ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት አመት በክልሎች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መሰራቱን እና በዚህም ውጤት መገኘቱንም አስታውቀዋል።   ለዚህ ከከፍተኛ አመራሩ ጀምሮ ለስራው ትኩረት ሰጥቶ ህብረተሰቡ የዲጂታል መታወቂያ እንዲመዘገብ በማድረግ በኩል ትልቅ ተግባር ተከናውኗል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ትምህርት ማህበረሰቡ የፋይዳ ዲጂታል ትግበራ በትምህርት ቤቶች ውጤታማ እንዲሆን ያከናወነውን ተግባር በተሞክሮነት ወደ ክልሎች የማስፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለጻ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት የዲጂታል አገልግሎቱን ለማሳለጥና ጠንካራ የሆነ የማንነት አስተዳደር ስርዓት ለመፍጠር እያገዘ ይገኛል፡፡
በክረምት በተከታተልነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስልጠና የቀሰምነው ዕውቀት በትምህርት ቤት ውጤታማ እንድንሆን አግዞናል
Jul 12, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የታዳጊዎች የክረምት ስልጠና የቀሰሙት ዕውቀት በትምህርት ቤት ውጤታማ እንዲሆኑ እንዳገዛቸው ቀደም ሲል የሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤ አይ) ስልጠና የተከታተሉ ታዳጊዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በተለያዩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች አራተኛውን የታዳጊዎች የክረምት ስልጠና በሳይንስ ሙዚየም አስጀምሯል። ስልጠናውን ተከታትለው የጨረሱ ታዳጊዎች ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ ቀደም ሲል የወሰዱት ስልጠና ህልማቸውን እውን ለማድረግ በሚሰሩት ስራ በብዙ መንገድ ደግፏቸዋል። በትምህርት ማዘመን የሚያስችል ፕሮጀክት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ወጣት ሰለሞን መብሬ የ2014 የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስልጠና ወስዶ አጠናቋል። እንደወጣት ሰለሞን ገለጻ፤ አሰልጣኞቹ በዘርፉ ያላቸው እውቀት ከፍተኛ በመሆኑ ፈጠራን ለመውደድና ለማሰብ አስችሏቸዋል። በዚህም የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ወደ ጥቅም መቀየር የሚያስችል አቅም ማዳበራቸውን ጠቁሞ፤ በተለይ በቡድን የመስራት መንፈስ እንዲላበሱ እንደረዳቸው ተናግሯል። የ12ኛ ክፍል ተማሪ ዲቦራ ወንድወሰን የ2015 የሰው ሰራሽ አስተውሎት የክረምት ስልጠና ተመራቂ ነች። በተከታተለቸው ስልጠና በአጭር ጊዜ ውስጥ አዳዲስ ነገሮች ለመገንዘብ መቻልዋን ተናግራለች። እንዲሁም በቡድን የመስራት ችሎታና ችግሮችን የመፍታት አቅም ለማዳበር እንደረዳትም ነው የገለፀችው። አስተያየት ሰጪዎቹ ስልጠናው የሀገር ብሎም የማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚያስችሉ መርሃ ግብሮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተናግረዋል። በዚህም የአራተኛውን ዙር የሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤአይ) የክረምት ስልጠና የሚወስዱ ታዳጊ ተማሪዎች ያገኙትን እድል በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል። በሌላ በኩል ዘንድሮ ወደ ስልጠናው የሚገቡ ሰልጣኞች በበኩላቸው፤ በስልጠናው የተሻለ እውቀትና ችሎታ አዳብረው ለመውጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ተማሪ ቅዱስ ሙሴ የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤአይ) መማር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን በማመን ወደ ስልጠናው መምጣቱን ተናግሯል። ታዳጊዎች እንደዚህ ዓይነት ስልጠናዎች መሳተፋቸው ትልቅ ህልም እንዲያልሙ ና ህልማቸውን በተጨባጭ በመተርጎም ከራሳቸው አልፈው ለሀገር እንዲተርፉ ይረዳል ብሏል። የስምንተኛ ክፍል ተማሪ ኑሃሚን ጥበቡ እንደምትናገረው፤ አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ ስራዎችን ቀለል ባለ መልኩ ለማከናወን የሚረዳ በመሆኑ ሥልጠናውን ለመከታተል ፍላጎት አሳድሮባታል። በዚህም ዘንድሮ በሚሰጠው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የክረምት ስልጠና በምታገኘው እውቀት ፓይለት የመሆን ህልሟን እውን ለማድረግ እንደሚያግዛት ታምናለች።
"ዙሪያ" የተሰኘው መተግበሪያ የንግድ ስርዓቱን በማቀላጠፍ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና ይኖረዋል - ኢትዮ ቴሌኮም
Jul 12, 2025 106
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ "ዙሪያ" የተሰኘው መተግበሪያ የንግድ ስርዓቱን በማቀላጠፍ፣ የተገልጋዮችን ጊዜና ገንዘብ በመቆጠብ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና ገለጹ። ኢትዮ ቴሌኮም፣ ዳሽን ባንክ እና ኢታ ሶሊዩሽን የንግድ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን የሚያቀላጥፍ "ዙሪያ" የተሰኘ የቢዝነስ አውቶሜሽን ሶሉሽን መተግበሪያ ይፋ አድርገዋል። የኢትዮ ቴሌኮም ችፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና እንዳሉት፣ መተግበሪያው የንግድ ስርዓቱን በማዘመን የተገልጋዮችን ጊዜና ገንዘብ የሚቆጥብ ነው። የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በቀላሉ ለማወቅ እንደሚረዳና ለነጋዴዎች የተሻለ የክፍያ መፈጸሚያ አማራጭ እንደሚሆን ጠቁመዋል። "ዙሪያ" ለአጠቃቃቀም ቀላል እና ፈጣን፣ ደህነንቱ የተረጋገጠ መሆኑንም ጨምረው አንስተዋል። የውጪ እና የሀገር ውስጥ የክፍያ ካርዶችን እንደሚቀበልና የሂሳብ ስራን ቀላል እንደሚያደርግም አስታውቀዋል። በወረቀትና በማሽን ይሰራ የነበረውን የክፍያ ስርዓት ወደ አንድ ወጥ አተገባበር የሚያመጣ መተግበሪያ እንደሆነም ጠቁመዋል። መተግበሪያው የንግድ ስርዓቱንና አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል።
ስፖርት
በሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ሩብ ፍጻሜውን የሚቀላቀሉ ቀሪ ሀገራት የሚለዩባቸው ጨዋታዎች ይደረጋሉ
Jul 14, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት የመጨረሻ መርሃ ግብር ዛሬ ይካሄዳል። ከምሽቱ 4 ሰዓት ደቡብ አፍሪካ ከማሊ በሆነር ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ደቡብ አፍሪካ እና ማሊ በተመሳሳይ አራት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል። የጨዋታው አሸናፊ የምድቡ መሪ በመሆን ሩብ ፍጻሜ መግባቱን ያረጋግጣል። አቻ መውጣት በሂሳባዊ ሁለቱን ቡድኖች ሩብ ፍጻሜውን እንዲቀላቀሉ የሚያስችላቸው እድል አለ። ሀገራቱ ከዚህ ቀደም ሁለት ጊዜ በውድድር ጨዋታዎች ተገናኝተው ደቡብ አፍሪካ ሁለቱንም ጨዋታዎች አሸንፋለች። ደቡብ አፍሪካ በጨዋታዎቹ ስድስት ግቦችን ስታስቆጥር ማሊ ምንም ግብ ከመረብ ላይ አላሳረፈችም። እ.አ.አ በ2010 በደቡብ አፍሪካ አስተጋጅነት በተካሄደው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ ተገናኝተው አዘጋጇ ሀገር ማሊን 4 ለ 0 አሸንፋለች። ቁጥራዊ መረጃዎች የደቡብ አፍሪካን የበላይነት ቢያሳዩም በጥሩ ወቅታዊ ብቃት ላይ የምትገኘው ማሊ በዛሬው ጨዋታ ጠንካራ ፉክክር እንደምታደርግ ይጠበቃል። በምድብ ሶስት ጋና ከታንዛንያ በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ በቤርካኔ ሙኒሲፓል ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ታንዛንያ እና ጋና በተመሳሳይ አንድ በግብ ክፍያ ተበላልጠው ሶስተኛና አራተኛ ደረጃን ይዘዋል። ሁለቱ ቡድኖች ወደ ሩብ ፍጻሜ ለመግባት ሶስት ነጥብ ማግኘት ግድ ይላቸዋል። ማሸነፍ ብቻ ሳይሆን የደቡብ አፍሪካ እና የማሊን ጨዋታ ውጤት ይጠብቃሉ። የጨዋታው አሸናፊ በሂሳባዊ ስሌት ምርጥ ሶስተኛ ወይም በቀጥታ ወደ ሩብ ፍጻሜ የመግባት እድል አለው። በሶስት ምድብ ተከፍሎ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ከየምድቡ አንደኛ እና ሁለተኛ የሚወጡ ሀገራት ለሩብ ፍጻሜ ያልፋሉ። ከምድቦቹ ምርጥ ሶስተኛ ሆነው የሚያጠናቅቁ ተጨማሪ ሁለት ሀገራት ሩብ ፍጻሜውን ይቀላቀላሉ።
ቼልሲ ፒኤስጂን ባልተጠበቀ ሁኔታ በማሸነፍ የዓለም ክለቦች ዋንጫን አሸነፈ
Jul 14, 2025 101
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ቼልሲ ፒኤስጂን 3 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሜትላይፍ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኮል ፓልመር ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ጆአኦ ፔድሮ ቀሪዋን ጎል ለሰማያዊዎቹ ከመረብ ላይ አሳርፏል። የፒኤስጂው ጆአኦ ኔቬስ በ86ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በጨዋታው ፒኤስጂ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢወስድም ቼልሲ ወደ ሜዳ ይዞ በገባው የመልሶ ማጥቃት እንቅስቃሴ ውጤታማ ሆኗል። ቼልሲ ኳስ በሚያዝበት አጋጣሚዎች ከተጋጣሚው የበለጠ አስፈሪ ነበር። የፒኤስጂ የመሐል ክፍል ተጫዋቾች እንደ ልባቸው እንዳይጫወቱ የማድረግ እቅድ ይዞ የገባው ቼልሲ የተሳካላት ሲሆን የፓሪሱን ክለብ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋቾች እንቅስቃሴ መግታት ችሏል። ሰማያዊዎቹ በመከላከሉ ረገድም የተዋጣላቸው ነበሩ። ቼልሲ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊውን በመርታት የዓለም ክለብ ዋንጫን አንስቷል። በጨዋታው ሁለት ጎል ያገባው እና አንድ ለግብ ያቀበለው ኮል ፓልመር የጨዋታ ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። ውጤቱ የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪ ያልተጠበቀው ነው። የፈረንሳዩ ቡድን ጨዋታውን ያሸንፋል የሚል ሰፊ የቅድሚያ ግምት አግኝቶ ነበር። የምዕራብ ለንደኑ ክለብ በዩኤፋ ኔሽንስ ሊግ ጨዋታው የዓለም ዋንጫ ክብር ጨምሯል። ፒኤስጂ በአስደናቂው የውድድር ዓመት ጉዞ አምስተኛው ዋንጫ የማንሳት ህልሙ አልተሳካም። ቼልሲ ከዋንጫው በተጨማሪ የ40 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሽልማት አግኝቷል። የቼልሲው ኮል ፓልመር የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች በመባል ተመርጧል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፍጻሜውን ጨዋታ በሜትላይፍ ስታዲየም ተገኝተው ተከታትለዋል።
አልጄሪያ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች
Jul 14, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት የመጨረሻ መርሃ ዛሬ ማምሻውን ተደርጓል። በላርቢ ዛውሊ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ናይጄሪያ እና አልጄሪያ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል። ውጤቱን ተከትሎ አልጄሪያ በአምስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ሩብ ፍጻሜ ገብታለች። አስቀድማ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለችው የዘጠኝ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ናይጄሪያ በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ ሆና አጠናቃለች። በዚሁ ምድብ በፔሬ ጄጎ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቦትስዋና ቱኒዚያን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ሌሴጎ ራዲያካንዮ እና ጋኦንያዲዌ ኦንትላሜትሴ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። የስሚን ካንቹች ለቱኒዚያ ብቸኛዋን ጎል አስቆጥራለች። ውጤቱን ተከትሎ ቦትስዋና በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ምርጥ ሶስተኛ ሆና ለማለፍ የነገ የምድብ ሶስት ጨዋታዎች ውጤት ትጠብቃለች። ቱኒዚያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
በሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ ሁለት የሚደረጉ ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Jul 13, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ። ናይጄሪያ ከአልጄሪያ በላርቢ ዛውሊ ስታዲየም፣ ቱኒዚያ ከቦትስዋና በፔሬ-ጄጎ ስታዲየም በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። የዘጠኝ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ናይጄሪያ በስድስት ነጥብ ወደ ሩብ ፍጻሜ መግባቷን ማረጋገጧ ይታወሳል። ማሸነፍ ወይም አቻ መውጣት የምድቡ መሪ ሆና እንድታጠናቅቅ ያስችላታል። በአራት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው አልጄሪያ ማሸነፍ በቀጥታ ወደ ሩብ ፍጻሜው ያስገባታል። ተሸንፋም ወይም አቻ ወጥታ ሁለተኛ ሆና ወይንም ምርጥ ሶስተኛ ሆና ልታልፍ ትችላለች። በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ቱኒዚያ ወደ ሩብ ፍጻሜው ለመግባት ማሸነፍ ግድ ይላታል። ለሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አራት ነጥብ በናይጄሪያና አልጄሪያ ጨዋታ ውጤት ላይ ተመስርታ ሁለተኛ ወይም ምርጥ ሶስተኛ ሆና ልታልፍ ትችላለች። ሁለት ሽንፈት አስተናግዳ ያለ ምንም ነጥብ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን የያዘችው ቦትስዋና ማሸነፍ ምርጥ ሶስተኛ ሆና እንድታልፍ የሚያደርግ እድል ሊሰጣት ይችላል።
አካባቢ ጥበቃ
የክረምቱ ዝናብ የሚፈጥረውን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀልበስ በትኩረት መስራት ይገባል-ኢንስቲትዩቱ
Jul 14, 2025 48
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦የክረምቱ ዝናብ የሚፈጥረውን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀልበስ በትኩረት መስራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ዝናቡ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የደቡብ ምዕራብ፣ምዕራብና ሰሜን ምዕራብ የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ዝናብ እንደሚኖር አመላክቷል። በምስራቅ፣ሰሜን ምስራቅ እና መካከለኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት እንደሚኖርም እንዲሁ። በሌላ በኩል በሰሜን ምስራቅ፤ መካከለኛው እና ምዕራብ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ አልፎ አልፎ ከሚጠናከሩ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በመነሳት ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር ጠቁሟል። የሚኖረው የዝናብ መጠን ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅሥቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንዳለው በማንሳት፤ የሚኖሩትን መልካም አጋጣሚዎች ለመጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀነስ መስራት እንደሚገባም ገልጿል። በሚኖረው የአየር ሁኔታ በአብዛኛው ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖር ኢንስቲትዩቱ በትንበያው ጠቅሷል። አልፎ አልፎ ከሚኖር ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች፣ የከተማም ሆነ የገጠር አካባቢዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ፣ የወንዞች ከፍታ መጨመር ሊያስከትል እንደሚችልም አስጠንቅቋል። በመሆኑም የሚመለከታቸው የዘርፉ አካላት ሊኖር የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀትና የማፅዳት ስራ መስራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥቷል።
''አካባቢን ፅዱ ለማድረግ በሚሰበሰብ ቆሻሻ ህይወት እንደሚለወጥ ማሳያው እኔ ነኝ''
Jul 13, 2025 112
ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ ከየአካባቢው የሚወጣውን ቆሻሻ በአግባቡ በመሰብሰብ ከራስ አልፎ ለሌሎች የስራ ዕድል መፍጠር እንደሚቻል የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው አቶ ሄኖክ ዶንጋቶ ራሳቸውን በዋቢነት ይጠቅሳሉ፡፡ አቶ ሄኖክ ዶንጋቶ በሀዋሳ ከተማ ቆሻሻ በመሰብሰብ ህይወታቸውን ቀይረው ለሌሎች የስራ ዕድል ያመቻቹ ግለሰብ ናቸው።     አቶ ሄኖክ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባል የነበሩና በግዳጅ ላይ በደረሰባቸው ጉዳት ያለስራ ቆይተው ኋላ ላይ በሀዋሳ ከተማ ቆሻሻን ወደ መሰብሰብ ስራ መግባታቸውን ይናገራሉ። ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ከየቤቱና ተቋማቱ የሚወጣውን ቆሻሻን የእጅ ጋሪን በመጠቀም በከተማው ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው “ ቆሻሻ ያለው!!! ቆሻሻ ያለው” በማለት የመሰብሰብ ስራ የየዕለት ተግባራቸው መሆኑን ይገልፃሉ። አሁን ላይ ከሀዋሳ ከተማ ከሚሰበሰበው አጠቃላይ የቆሻሻ መጠን 35 በመቶ የሚሆነውን እየሰበሰቡ መሆኑን ያስረዱት አቶ ሄኖክ ከየሰፈሩ በሚወጣው ቆሻሻ ጥቅም ማግኘት ብቻም ሳይሆን አካባቢው ፀድቶ ሲመለከቱት ከፍተኛ እርካታ እንደሚሰማቸው ይናገራሉ።   በቆሻሻ መሰብሰብ ስራው ላይ በመሰማራታቸው ከወዳጆቻቸው ከፍተኛ ትችት ቢገጥማቸውም "የሚጠቅመኝን የማውቀው እኔ ነኝ፤ በማለት በትጋት በመስራት ከራሴ አልፌ ለሌሎች የስራ ዕድልን መፍጠር ችያለሁ'' በማለት ምላሽ ይሰጣሉ።፡ በ2010 ዓ.ም ሌሎች 12 የቤተሰብ አባላትን በመያዝ ህጋዊ ዕውቅና ያለው ማህበር መመስረታቸውን ያወሱት አቶ ሄኖክ "ቆሻሻን ወደ ሀብትነት በመቀየር ከራሳችን አልፈን ለበርካቶች የስራ ዕድል ፈጥረናል" ሲሉም ያክላሉ፡፡ ማህበሩ ከ134 በላይ ለሚሆኑ ሰራተኞች ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠሩን ገልፀው ቆሻሻን ከተለያዩ አካባቢዎች በማሰባሰብ ወደ ማህበሩ የሚያቀርቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የገቢ ምንጭ መሆን መቻሉንም አውስተዋል፡፡ ከከተማው ከሚሰበሰበው ቆሻሻ የማይበሰብሰውን የፕላስቲክ ምርት በመጭመቅ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውል ወደ አዲስ አበባ ከመላክ ባሻገር በተፈጥሮ ማዳበሪያ ሽያጭ ማህበሩ ወደ 300 ሺህ ብር የሚጠጋ ገቢ ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡ የአቶ ሄኖክ ባለቤት ወይዘሮ መሰረት ድጋሎ ''ቆሻሻን ብዙዎች የሚጸየፉት ቢሆንም ለእኛ ግን ህይወታችንን የቀየርንበትና ለብዙዎች የስራ ዕድል የፈጠርንበት የገቢ ምንጫችን ነው'' ብለዋል፡፡   ማህበሩ ቆሻሻ በአግባቡ ከተያዘ ሀብት መሆኑን በተጨባጭ እያሳየ ነው ያሉት ደግሞ የማህበሩ ኃላፊ አቶ አልታዬ ቦቦላ ናቸው። ማህበሩ ከቆሻሻ ገቢ ከማግኘት ባለፈ ሀገራዊ የጽዳት ስራ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል፡፡   ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ በሀዋሳ ከተማና ሌሎች ወኪሎች ባሉባቸው ከተሞች ከግለሰቦች መኖሪያ ቤት፣ ከሆቴሎችና ከተለያዩ ድርጅቶችና ፋብሪካዎች ቆሻሻን በመሰብሰብና በመለየት የፕላስቲክ ቆሻሻ በተፈጥሮ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት እየተከላከሉ እንደሚገኙም ገልፀዋል። ቆሻሻን ሰብስቦ ወደ ሀብትነት በመቀየር ሂደት ትልቁ ተግዳሮት "ቆሻሻን ለይቶ የማስቀመጥ ባህል ያለማደግ ነው" ያሉት አቶ አልታዬ በዚህ ላይ ግንዛቤን መፍጠር እኛን ጨምሮ ከሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ይጠበቃል ብለዋል። በማህበሩ የስራ ዕድል ከተፈጠረላቸው መካከል አቶ አዲሱ ኩኬ ከመንግስት ስራ በጡረታ ከተገለሉበት ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ በዚህ ማህበር በመቀጠር ቤተሰባቸውን በኢኮኖሚ የሚደጉሙበት ዕድል እንዳገኙ ተናግረዋል፡፡   በሲዳማ ክልል ደን አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን የአከባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ቲቦ በክልሉ ከፕላስቲክ ብክለት የጸዳ አካባቢን ለመፍጠር በተቀናጀ መንገድ እየተሰራ ነው ብለዋል::   ከቆሻሻ የጸዳ አካባቢ ለመፍጠር በሚደረግ ጥረት ከግንዛቤና ቆሻሻን ለይቶ ከመሰብሰብና መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ከማድረግ አንፃር ተግባሩ ተጠናክሮ እየተከናወነ መሆኑን ነው አቶ ዮሴፍ ያነሱት::  
በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የማከናወኑ ተግባር ይጠናከራል - ሚኒስትር መላኩ አለበል
Jul 12, 2025 106
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የማከናወኑ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ተናገሩ፡፡ ሚኒስትሩና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እንቅስቃሴን የተመለከቱ ሲሆን፤ ችግኝ በመትከልም አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡   በዚህ ወቅት ሚኒስትሩ በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተቀናጁ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ከአየር ንብረት ጋር የተስማማ ሁኔታ እንዲኖር የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ስራ እየተስፋፋ ነው። ዛሬም በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተከናወነው የዚህ አካል መሆኑን አንስተው፤ በቀጣይም ይህንን የበለጠ እያጠናከርን እንሄዳለን ብለዋል። ጠንክሮ በመስራትና ኢኮኖሚኖዋን በማሻሻል ኢትዮጵያ እንደምታንሰራራ ያመለከቱት ሚኒስትሩ፤ የምንተክለውም መልካም ዘር ነው፤ የኢትዮጵያን የወደፊት ተስፋን የሚያለምለምና የስራ ባህልን ታሳቢ ያደረገ ነው ሲሉ ተናግረዋል። "በመትከል ማንሰራራት" የሚለው ቁልፍ መልዕክትም እነዚህን ሁሉ ያየዘ በመሆኑ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኢንዱስትሪዎች የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ሀይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ሁሉ ስራ የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የችግኝ ተከላ ልዩ ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል፡፡ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብሩ የሚተከለው ችግኝ ለምግብነት፣ ለፋብሪካ ግብዓትና ለማገዶ ጨምሮ አካባቢው ለኑሮና ለስራ የተመቸ ከማድረግ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ፓርኮች ይህን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል፡፡ የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ አራርሶ ገረመው(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተሰማሩ ከ8 በላይ ካምፓኒዎች የግብርና ምርቶች በማቀነባበር ላይ መሰማራታቸውን ተናግረዋል። ፓርኩን ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችል የድጋፍና ክትትል ውይይት መደረጉን ተናግረው፤ ችግኝ በመትከል የፓርኩን ስራ ለማጠናከር የሚያግዝ ዐሻራ ማኖራቸውንም አንስተዋል፡፡ በፓርኩ የስራ ዕድልና የገበያ ትስስርን በመፍጠር እንዲሁም የግብርና ቴክኖሎጂ በማሸጋገር ረገድ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ መኖሩን የገለጹት የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሀይሉ ዬተራ ናቸው፡፡ ከ137ሺህ በላይ አርሶ አደሮች የምርት አቅርቦት ትስስር መፈጠሩንም ጠቅሰዋል፡፡
አረንጓዴ ዐሻራ የነገዋን ኢትዮጵያ ለትውልዱ ምቹና የተሻለች የሚያደርግ ነው
Jul 12, 2025 90
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ ዐሻራ የነገዋን ኢትዮጵያ ለትውልዱ ምቹና የተሻለች የሚያደርግ መሆኑን የነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ሰልጣኞች እና የባለድርሻ ተቋማት ኃላፊዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል፡፡ የነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ሃላፊዎች፣ ሰልጣኞች እና ባለድርሻ አካላት በማዕከሉ ግቢ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። የቀድሞ የአዲስ አበባ ማኅበራዊ ትረስት ፈንድ ዋና ዳይሬክተር አስራት ንጉሤ በዚሁ ወቅት፤ አረንጓዴ ዐሻራ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ከመከላከል ጀምሮ በርካታ ትሩፋቶችን እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በነገዋ የሴቶች የተሃድሶና የልህቀት ማዕከል የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር መከናወኑ ትልቅ ፋይዳ አለው ነው ያሉት። በማዕከሉ ያሉ ሴቶች ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡና ዐሻራቸውን የሚያሳርፉበት እድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በስልጠና ቆይታቸው ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ ስለአረንጓዴ ልማት ተግባራዊ ግንዛቤ እንደሚያገኙበትም አንስተዋል። የነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ምክትል ዳይሬክተር ልኬ ኃይለማርያም በበኩላቸው፤ በዛሬው የአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ-ግብር ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ ችግኞችን ከመትከል ባለፈ ፀድቀው ለፍሬ እንዲበቁ በማዕከሉ ወስጥ የሚገኙ ሰልጣኞችን በማሳተፍ የመንከባከብ ሥራ እንደሚሰራ ገልፀዋል። የማዕከሉ ግቢ በአረንጓዴ ልማት የሚታወቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬው ችግኝ ተከላም ገጽታውን ይበልጥ የሚያጎላ ነው ብለዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ከተሳተፉት ባለድርሻ አካላት መካከል የታፍ ኢነርጂ የቦርድ አባል የሆኑት ኤልሳቤጥ ፈታሂ፤ ድርጅቱ ለምግብነት የሚያገለግሉ የፓፓዬ፣ የአፕልና የአቮካዶ ችግኞችን በነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ግቢ መትከሉን ገልጸዋል፡፡ ችግኞቹ የተተከሉበት ቦታ ለመንከባከብ አመቺ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ችግኞችን እንደሚንከባከቡም ተናግረዋል፡፡ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት የመርኃ-ግብሩ ተሳታፊዎች መካከል ዶክተር ፍስሃ ዋሱ እና እየሩሳሌም አንዷለም በአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ-ግብር ችግኞችን በመትከላቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል። በነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ችግኝ የተከለችው ሰልጣኝ እየሩሳሌም አንዷለም እንደገለጸችው፤ አረንጓዴ ዐሻራ ለመጪው ትውልድ ጉልህ ፋይዳ አለው። በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉት ችግኞች ለፍሬ እንዲበቁ እንክብካቤ እንደምታደርግ ነው የተናገረችው፡፡ ከታፍ ኢነርጂ የመጡት ዶክተር ፍስሃ ዋሱ በበኩላቸው፤ አረንጓዴ ዐሻራ ለትውልዱ ምቹና ሥነ-ምኅዳሯ የተጠበቀ ሀገር ለማስረከብ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። በዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱ ይታወቃል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 961
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ።   በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1331
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል።   የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 995
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል።   ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1623
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
የህንድ የፈጠራ ማዕከል - ባንጋሎሩ
Jul 2, 2025 469
ቤተልሄም ባህሩ(ኢዜአ) የዴልሂና አግራ ቆይታችንን ጨርሰን ወደ ቀጣይ መዳረሻችን ባንጋሎሩ ከተማ ልንጓዝ ስንሰናዳ አብዛኛው የጋዜጠኛ ልዑክ ያሳሰበው እንደሰም የምታቀልጠውን የአግራ ፀሀይና ሙቀት በባንጋሎሩም ታገኘን ይሆን? የሚለው ነበር። ሆኖም ከዴልሂ ኢንድራ ጋንዲ አየር ማረፊያ ተነስተን ለሶስት ሰዓት ከተቃረበ በረራ በኋላ ያገኘናት ባንጋሎሩ የተለየች ሆነን አገኘናት። ባንጋሎሩ ቀዝቀዝ ባለ አየር ነበር እንግዶቿን የተቀበለችን። በዕለቱ ከክፍሎቻችን ወጥተን በጋራ ወደአየር ማረፊያ የሚወስደንን ትራንስፖርት ስንጠባበቅ ከጋዜጠኛ ቡድኑ ስድስት አባላት ከአጠገባችን እንዳልነበሩ አስተዋልን። የት ጋር እንደተነጣጠልን አላስታውስም። በዚህ ምክንያት ግን የእለቱ ጉዟችን ተሰርዞ ከተማዋን ለማየት ስንዘዋወር የማውቀው ዓይነት እንጂ የተለየ ሙቀት አላስተናገድኩም። የ13 ወር ፀጋ በመባል የምትታወቀው አገሬ ኢትዮጵያ ከዳሎል እስከ ራስ ዳሽን ባላት የመልከዓ ምድር አቀማመጥና ልዩ ልዩ የአየር ጠባይ ሙቀቱንም፣ ቅዝቃዜውንም ማወቃችን እንደዚህ ለአለ አጋጣሚ መልካም ስሜት ይፈጥራል። በተወሰነ ደረጃ በህንድ ያጋጠመኝ የአየር ባህሪ ከአገሬ ጋር ቢመሳሰልብኝ የፈጣሪንና የተፈጥሮን ስራ አጃኢብ ብዬ እንዳልፍ አድርጎኛል። ባንጋሎሩ ከተማ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የህንድ ሲልከን ቫሊ በመባል ትታወቃለች። ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎችም ከመገለጫዎቿ መካከል ናቸው። የጠፈር ጠበብቶቹ - ባንጋሎሩ ደርሰን በመጀመሪያ ያየነው ዓለም በስፔስ ሳይንስ እየሰራች ያለችውና እያስመዘገበችው የምትገኘው ውጤት ማሳያ የሆነውን የህንድ ስፔስ ምርምር ድርጅትን ነው። ተቋሙ የህንድ መንግስት የስፔስ ዲፓርትመንት አካል ሲሆን፤ ዶክተር ቪክራም ሳራብሃይ በተሰኙ ባለራዕይ በ1962 የተወጠነና አሁን ላይ በዘርፉ ተገዳዳሪ መሆን የቻለ ነው። የተቋሙ ዓላማ የስፔስ ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመተግበር ለተለያዩ አገራዊ ጥቅሞች ማዋል መሆኑን ተከትሎ የሳተላይት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማምረት ስራን ጨምሮ ከአገሩ አልፎ ለሌሎች አገራትም በዘርፉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። የተደረገልን ገለፃ አብዛኛውን ጋዜጠኛ ያስደመመ ነበር ከገለፃ በኋላ በጋዜጠኞች የተነሳው ሃሳብም ህንድ በስፔስ ዘርፍ ያላት ልምድና ያከናወነችው ተግባር በቀጣይም ልትሰራ የወጠነቻቸው ሃሳቦች የአገሪቱን መዳረሻ የተለሙ በአገራቸው እንዲተገበር የሚናፍቁት መሆኑን ነው። ተቋሙ በዘርፉ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን የሚያጠናክር መሆኑን ከተደረገልን ገለፃ ተገንዝበናል።   በሳይንስ፣ ኢንጂነሪንግና አስተዳደር ምሁራንን በማስተማር እያበረከተ ያለው የህንድ የሳይንስ ኢንስቲትዩት በባንጋሎሩ ከጎበኘናቸው መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የተውጣጡ ተማሪዎችን የሚያስተምርና ከተቋማት ጋርም በዘርፉ የሚሰራ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ከጅማ፣ በተግባር ለመቀየር ሲታትሩ የስታርት አፖችን የምርት ውጤቶቻቸውን ሲፈትሹና ሲሞክሩ ተመልክቻለሁ። በኢትዮጵያም አሁን ላይ ለስታርት አፖች በተሰጠው ትኩረትና በተፈጠረው ምቹ ስነ ምህዳር የፈጠራ ውጤቶች እያደጉና እየተበራከቱ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። እንደ አዳማና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት የተማሪዎችን ፈጠራ ወደ ውጤት ለመቀየር እየተጉ መሆኑና የስታርት አፕ ኤግዚቢሽንና የሰመር ቡት ካምፖች ፈጠራን ምን ያህል እያበራከቱ መሆናቸው በጉብኝቱ ወቅት ወደ አዕምሮዬ የመጣ የአገሬው ህዝብ በውጤት የታጀበ ጥረት ነው።   ከአራት አስርት ዓመታት በላይ በባዩቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘው ባዮኮንም ከባላንጎሩ የጉብኝት መዳረሻችን መካከል የሆነና አስፈላጊ መድሀኒቶችን የሚያመርትና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይም እየሰራ ያለ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተጠቃሚ ናቸው። ከ120 በላይ በሆኑ አገራት ለስኳርና ካንሰር ህመም የሚያገለገሉ መድሀኒቶችን በማምረትና በማሰራጨት ለህሙማን ፈውስና ለጤናው ዘርፍ ስርዓት አስተዋፅኦ እያበረከተም ይገኛል። የተቋሙ ላቦራቶሪና ዘመኑን የዋጀና ደረጃውን የጠበቀ ማምረቻ ፋብሪካን መጎብኘቴ አለም በፋርማሲዩቲካልስ ዘርፍ ያለችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። የባንጋሎሩ ቤተመንግስት - ይህን ቤተ መንግስት ማስቃኘቴን ከመጀመሬ በፊት በስፍራው ካስገረመኝ ነገር ላወጋችሁ ወደድኩ። ቤተ መንግስቱን ለመጎብኘት ያቀናነው በእለተ ሰኞ ነበር። ሆኖም ምድረ ግቢውን ቃኝተን ስለህንፃው ሰምተን ከመመለስ ውጪ ወደ ውስጥ አልዘለቅንም። ለምን? ለሚለው ምላሹ በዚህ ስፍራ "ሰኞ የእረፍት ቀን ናት" ነው። እንዴት ካላችሁ ቤተ መንግስቱ ቅዳሜና እሁድ በበርካታ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑን ተከትሎ በስፍራው ለሚሰሩ ሰራተኞች የእረፍት ቀናቸው ሰኞ በመሆኑ ነው። የቤተ መንግስቱ ምድረ ግቢ ሰፊና ልምላሜ የተላበሰ ሲሆን፤ የሚያምርና ለዓይን የሚስብ ኪነ ህንፃ ያለው ነው። አሰራሩና ውጥኑም እንደሚከተለው ነው። በዎዲየር ስርወ መንግስት ንጉስ ቻማራጃ ዋዲያር ወደ እንግሊዝ ባደረጉት ጉዞ በለንደን ዊንሶር ግንብ ይደነቃል። ተደንቆም አልቀረ የባንጋሎሩ ቤተ መንግስትን በተመሳሳይ ሁኔታ ይገነባል። ይህ ቤተ መንግስት በተወሰነ መልኩ የመካከለኛው ዘመን የኖርማንሲና የእንግሊዝ ግንቦችን ይመስላል።   ቪድሃና ሶውዳ የካራንታካ ህግ አውጪ አካል መናገሻ በጉብኝታችን ያየነው ሌላው መዳረሻ ስፍራችን ነው። የህግ አውጪና የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የያዘው ይህ ህንፃ ህንድ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ በራሷ መሀንዲስ የሰራችው የመጀመሪያው ህንፃ መሆኑ ተገልፆልናል። የህንፃ ግንባታ ጥበብ ማሳያ፣ የፖለቲካ መናገሻ እንዲሁም የባህል ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል።   እንደአጠቃላይ በቆይታዬ የተመለከትኩት የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ማበረታቻ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራ ኢትዮጵያ እያከናወነች ካለው የኮሪደር ልማትና ስታርት አፕን የማበረታታት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ምቹነት ስራዎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ነው። በህንድና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ዘመናትን የተሻገረ፤ ለሁለት ሺህ ዓመታት የዘለቀ መሆኑን የታሪክ መዛግብት ያሳያል። የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት በአክሱም ስርወ መንግስት ኢትዮጵያና ህንድ በአዱሊስ ወደብ በኩል የንግድ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያ ቅመማ ቅመምና ሐርን ከህንድ ትገበይ ነበር። ህንድ ደግሞ ወርቅና የዝሆን ጥርስን ከኢትዮጵያ ትሸምት ነበር። ህንድ ከንግድ ልውውጥ ባሻገር በኢትዮጵያ ኪነ ህንፃ ግንባታ ላይ አሻራዋን አኑራለች። በኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍም ትልቅ አበርክቶ ያላት አገር ናት። ህንድ ነፃነቷን ካገኘችበት እኤአ 1948 አንስቶ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት ኢትዮጵያና ህንድ ሌላው የሚያመሳስላቸው ነገር ሆኖ ያገኘሁት የአምራች ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያከናወኑ ያሉት ንቅናቄ ነው። ህንድ እ.አ.አ ከ2014 ጀምሮ የአምራች ዘርፉን ለማበረታታት "ሜድ ኢን ኢንዲያ" በሚል ለአስር ዓመት የተገበረችውና በርካታ ለውጥ የተመዘገበበት ንቅናቄ በኢትዮጵያ ከ2014ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ካለውና የሃገር በቀል ምርቶች እና አምራቾችን ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪያል ማህበረሰብ ግንባታን ማሳደግ ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢ መፍጠር እና የጥናት እና ምርምር ችግር ፈቺነትን ማሳደግን ዓላማ ካደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጋር የተመሳሰለ ነው። ንቅናቄ በኢትዮጵያ መተግበሩ ዓመታዊ የዘርፍ ዕድገት፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና ገቢ ምርት በመተካት በኩል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑም ይታወቃል። በህንድ ተዘዋውሬ በተመለከትካቸው ከተማዎች ባሉ ጎዳናዎች ከታዘብኩት ነገር ሰዎች ከሱቅ ለሚገበያዩት ነገር ሳይቀር በዲጂታል መንገድ ክፍያ መፈፀማቸውን ነው። በባጃጅና በሞተር የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘትም ጭምር ሞባይሉን በመጠቀም “ይህ ቦታ የት ነው?” ሳይል ያሻዎት ስፍራ መድረስም ሌላው ትዝብቴ ነው። ይህ ነገር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትኩረት አግኝተው እየተሰራባቸው ካሉት የዲጂታል ክፍያና ዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ መርሃ ግብር ጋር የሚመሳሰል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በቆይታችን ልክ እንደአትሌቶቻችን ሁሉ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርጎ የሚያስነሳውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝናና ክብር ለማስተዋል ችያለሁ። ፀጉረ ልውጥ መሆናችንን የተገነዘቡ በገበያ ማዕከላት የሚያገኙን እንዲሁም በምንጎበኛቸው ተቋማት የምንተዋወቃቸው ህንዳውያን "ከየት ናችሁ?" ብለው ሲጠይቁ፤ ለእኔና አንድ ከሌላ መገናኛ ብዙሃን የሄድን "ከኢትዮጵያዊ" ስንል የሚከተልልን ምላሽ "አሃ የኢትዮጵያ አየር መንገድ" የሚል ነው። ይህም አየር መንገዱ ስሙ ከኢትዮጵያ ተሰናስሎ የሚጠራ የአገሪቷ መታወቂያ ተቋም መሆኑን ያስገነዘበኝ ነው። ከህንዳውያን ጋር ብቻ ሳይሆን አብረን ከተጓዝን ጋዜጠኞች አንዱ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእናንተ የብቻ ሳይሆን እኛንም እንደራሳችን ሆኖ እያገለገለን ያለ የጋራ አየር መንገዳችን ነው" ሲል ነው የገለፀው። ይሄ ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገር ኩራት ብቻ ሳይሆን መለያ ምልክትም ጭምር መሆኑን የተረዳሁበት አጋጣሚ ነው። በቀናት ቆይታዬ በእንግዳ አክባሪነታቸውና በለገሱን ፍቅርና እንክብካቤ ከአገሬ የራቅኩ ያህል ሳይሰማኝ ብቸኝነትን ሳላስተናግድ እንደውም እየናፈኳቸው እንድመለስ ላደረጉኝ ህንዳውያን በከበረ ሰላምታ ላመሰግን እወዳለሁ።
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 468
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል።   ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል።   የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው።   የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው።   ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።    
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 1005
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች።   የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች።   ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ።   ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።      
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 1125
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 3418
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 2834
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 3015
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 4131
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2715
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2390
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3844
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48595
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43993
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 28094
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25445
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 23682
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 21807
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 21668
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 21298
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48595
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43993
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 28094
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25445
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ከሮም እስከ አዲስ አበባ 
Jul 11, 2025 207
ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ይካሔዳል። የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ኢንቨስትመንት እና ፋይናንስ፣ የምግብ ስርዓት ሽግግር ሁለንተናዊነትና የተገቡ ቃሎችን ከመፈጸም አንጻር ያለውን የተጠያቂነት ስርዓት ማጠናከር ጉባኤው ትኩረት ያሚያደርግባቸው ሀሳቦች ናቸው። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተምግብ ጉባኤ በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በጣልያን ሮም የተካሄደው የመጀመሪያ የተመድ ስርዓት ምግብ ላይ የተገቡ ቃሎች ትግበራ ሂደትን መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ነው። በመጀመሪያው ጉባኤ ላይ የ182 ሀገራት ተወካዮች፣ 21 የሀገራት መሪዎች እና 126 ሚኒስትሮችን ጨምሮ 3 ሺህ 300 ተሳታፊዎች ታድመውበታል። በጉባኤው ላይ የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሀገራት እና ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ስድስት የትኩረት አቅጣጫዎችን ይፋ አድርገው ነበር።   የምግብ ስርዓት ስትራቴጂዎችን ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር፣ ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓት አስተዳደር መገንባት፣ በጥናት፣ ዳታ፣ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ ሁሉን አቀፍ የእቅድ ዝግጅት እና ትግበራን ማጠናከር፣ በምግብ ስርዓት ውስጥ የንግዱ ማህበረሰብ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የአጭርና የረጅም ጊዜ የአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ ከትኩረት አቅጣጫዎቹ መካከል ይጠቀሳሉ። ኢንቨስትመንት፣ የበጀት ድጋፍ እና የእዳ አስተዳደር ሌላኛው የትኩረት መስክ ነው። በጉባኤው ላይ 300 ገደማ በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የምግብ ስርዓት ሽግግርን እውን ለማድረግ ቃል መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያመለክታል። በተለይም እ.አ.አ 2030 የማይበገር፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የምግብ ስርዓት መገንባት እንዲሁም ምግብ ለሁሉም የሚለውን ግብ ለማሳካት ጥረት እንደሚያደርጉ ሀገራት ቃል ገብተዋል።   ሁሉን አሳታፊ ነው በሚል አድናቆት ያገኘው ጉባኤው በስርዓት ምግብ ላይ ግንዛቤን ከማሳደግ እና አቅምን ከመገንባት አንጻር ውጤታማ እንደነበር ይነሳል። የምግብ ስርዓት ሽግግር አንገብጋቢና ጊዜ የማይሰጥ ጉዳይ እንደሆነም በጉባኤው ተወስቷል። ኢትዮጵያም በስርዓተ-ምግብ ጉባኤው ላይ የነበራት ተሳትፎ ስኬታማ ነበር። በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ውጤታማ እንቅስቃሴዎችን የሚያሳዩ ልምደችን አቅርባለች። በጉባኤው ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ግብርናን በማዘመን የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና በስርዓተ ምግብ ሽግግር ለማምጣት እየወሰደች ባለው የፖሊሲ እርምጃና ውጤቶች ዙሪያ ገለጻ አድርገውም ነበር። ኢትዮጵያ የኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት፣ ለየስነ ምህዳሩ ተስማሚ የሆኑ የተሻሻሉ ዝርያዎችን፣ አነስተኛ ቴክኖሎጂዎችንና ሌሎች ግብአቶችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለኢኮኖሚው ዕድገት የላቀ አበርክቶ እንዲኖረው እየሰራች መሆኑንም አንስተዋል።   በአረንጓዴ አሻራ፣ በበጋ መስኖ በተለይም በበጋ ስንዴ ምርት እና በሌማት ትሩፋት እየተገኙ ያሉ ውጤቶችን ለጉባኤው አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የስራ እድል ፈጠራን ለማበረታታትም ሆነ በስርዓተ-ምግብ ሽግግር ለማድረግ አዲስና የተለየ የፋይናንስ ሞዴል ያስፋልጋል በማለት በአጽንኦት ተናግረዋል። ዘላቂና አካታች የስርዓተ ምግብ ሽግግር አቅጣጫዎች ጥሩ አፈጻጸም የታየባቸው ቢሆንም በፋይናንስ አቅርቦት፣ በዓለም አቀፍ ትብብር፣ በአየር ንብረት ለውጥና በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመቋቋም በትብብር በመስራት በኩል በርካታ ችግሮች መስተዋላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የገለጹት። በመሆኑም ሀገሮች በስርዓተ ምግብ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በአነስተኛ እርሻ ስር-ነቀል ለውጥ በማምጣት ሽግግሩን ማፋጠን እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፅንኦት አንስተዋል። ለዚህም የሴቶችና የወጣቶች ተሳትፎን እንዲያሳድጉና ለግብርና ቴክኖሎጂ መስፋፋት እንዲሰሩ ጠይቀዋል ። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ-ምግብ ጉባኤ የመጀመሪያውን ጉባኤ መነሻ በማድረግ በተለያዩ አጀንዳዎች ይመክራል። ቀዳሚ ትኩረቱ ከመጀመሪያው ጉባኤው በኋላ የምግብ ስርዓትን አስመለክቶ ያሉ ለውጦች ምንድን ናቸው? የሚለው ነው። በጉባኤው ላይ ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን አስመልክቶ ያገኟቸውን ስኬቶች እና የጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ሪፖርት ያቀርባሉ። በተለይም የምግብ ስርዓት ሽግግሩ ሁለንተናዊነት እና ሁሉን አሳታፊነት ዋንኛ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ሁለተኛው የጉባኤው አጀንዳ በመንግስታት፣ የምግብ አምራቾች፣ የንግድ ማህበረሰቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር ነው። የባለድርሻ አካላት ትብብር መጠናከር የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንዳለው ታምኖበታል። በተጨማሪም ሀገራት እና ተቋማት በሮሙ ጉባኤ የገቧቸው ቃሎች የደረሱበትን ደረጃ የሚገመገም ሲሆን ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎም ይጠበቃል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት እና የኢንቨስትመንት መጠንን መጨመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ጉባኤው ይመክራል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር ስራዎች በአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ፣ አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም እና ሀገር በቀል የፋይናንስ መሰብሰብ አቅምን ማጎልበት ላይ ምክክሮች ይደረጋሉ ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ በሮም በነበረው ጉባኤው ላይ ይፋ ያደረጓቸው ስድስት የትኩረት መስኮች አፈጻጸም ግምገማ ሌላኛው አጀንዳ ነው። በአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ የሚካሄደው ሁለተኛው የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ የሀገራት መሪዎች እና ተወካዮች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ አርሶ አደሮች፣ አምራቾች እና የምግብ ስርዓት ሽግግር ተዋንያንን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። በጉባኤው ላይ ከዋናው ሁነት ጎን ለጎን የምግብ ስርዓት ትራስፎርሜሽን እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን አስመልክቶ በርካታ የጎንዮሽ ስብስባዎች ይደረጋሉ። ኢትዮጵያ በምግብ ስርዓት ሽግግር ያከናወናቸውን ስራዎች አስመልክቶም በጉባኤው ተሳታፊዎች የመስክ ምልከታ ይደረጋል። ኢትዮጵያ በስርዓት ምግብ ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እና በግብርናው ዘርፍ ባደረጋቻቸው ሀገር በቀል ሪፎርሞች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ጉባኤውን እንድታስተናግድ የተመረጥችባቸው ምክንያቶች ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር እየተወጣች ያለው የመሪነት ሚና እና በማደግ ላይ ከሚገኙ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ተምሳሌት የሆነች ሀገር መሆኗ ተመድ ዓለም አቀፉን ከፍተኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ እንዲያደርግ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማሳካት እያከናወነች ባለው ተግባር ዙሪያ ተሞክሮዋን ለዓለም ማህበረሰብ የማስገንዘብ ስራ ታከናውናለች። ተባባሪ አዘጋጇ ጣልያን እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ በምግብ ስርዓት ሽግግር ውጤታማ ተሞክሮ ያላት ሀገር ናት። የደቡብ አውሮፓዊቷ ሀገር ከኢትዮዮጵያ ጋር በመሆን ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን እየሰራችም ትገኛለች። ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎች ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እየጠበቀች ትገኛለች።  
በቻይና ይህም አለ!
Jul 8, 2025 273
  በአብነት ታደሰ በርግጥ ከዓለማችን የጥንት ስልጣኔ ምድሮች አንዷ ናት- ቻይና። በታሪክ ገጾች ‘የግኝት ምድር’(Land of Invention) የሚል ተቀፅላ የሰፈረላት የሺህ ዘመናት ባለታሪክ ሀገር። የጥንት ቻይኖች አያሌ ‘ግኝቶችን’ ለዓለም አካፍለዋል። ወረቀት ፈብርከው ዘመናቸውን ጽፈዋል፣ ማተሚያ ቁስ ፈጥረው አትመዋል፤ ኮምፓስ ፈልስመው አቅጣጫ ጠቁመዋል።በ221 ዓመተ-ዓለም አንድ ወጥ ስርወ መንግስት መስርተው በሀገረ መንግስት የታሪክ ዑደት ከፍታንም ዝቅታንም አይተዋል። በቻይና አያሌ ስርወ መንግስታት ተፈራርቀዋል። ቻይናውያን ክፉውንም ደጉንም ችለው አልፋዋል። የሕዝቡ ጽናት፣ ጥበብ፣ ቱባ ባህል፣ ታሪክና ብልሃት በቻይና ግንብ ይመሰላል። ግንቡም ዝም ብሎ የጡብ ክምር አይደለም፤ የመሰረተ-ጽኑነታቸው ትዕምርት(symbol) እንጂ። ሲሶውን ሕዝቧ በያንግትዝ ወንዝ ተፋሰስ ጉያ አቅፋ፣ ጥንተ ማንነቷን ሸክፋ ዕልፍ ዘመናትን ተሻግራለች። የቻይና ስርወ መንግስታት ከስመው የዛሬዋ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ ቻይና ከተመሰረተች ገና አንድ ምዕተ ዓመቷ ነው። ቅድመ ልደተ ክርስቶት በ221 ዓመተ-ዓለም የተመሰረተው ወጥ-ስርዎ መንግስት በመልከ ብዙ ምክንያቶች ተዳከመ። በፈረንጆቹ 1912 የመጨረሻው የቻይና ስርዎ መንግስት ተንኮታኮተ። ዘመናዊቷ የቻይና ሪፐብሊክ በዚህ ዘመን ተመሰረተች። ዳሩ ለውጡ አልጋ በአልጋ አልሆነም። ለሺህ ዘመን የጽኑ ስርዓተ መንግስት ባለቤቷ ሀገር ቻይና በአስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት ታመሰች። ወረራንም፣ ዕልቂትንም አስተናገደች። በዘመኑ ማኦ ዘዶንግ የሚባል ባለራዕይ መሪ በቻይና ምድር ተነሳ። አርቆ አሰበ፤ ሀሳቡንም አሰረጸ፤ በዓላማ ጸንቶ ክፉ ዘመን ተሻገረ። ማኦ እና ተከታዮቹ ለቻይና ትንሳኤ ታተሩ። በጽናት ታገሉ። ለመስዕዋትነት ቆርጠው ተነሱ፤ ዋጋም ከፈሉ። በአውሮፓዊኑ ዘመን አቆጣጣር በ1949 የዛሬዋን የቻይና ሕዝባዊ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ መሰረተ። ሃሳቡን ወደ ፖሊሲ ቀየረ፤ ተገበረውም። ቻይናን በኢንዱስትሪና ግብርና ምርት በንቅናቄ የማስፈንጠር ፕሮግራምንም (Great Leap Forward) ገቢራዊ አደረገ። ሆኖም ፖሊሲው በአንዴ ፍሬ አላፈራም። በወቅቱ በተፈጥሯዊና በሌሎች ምክንያቶች ቻይና በረሀብ ጠኔ ተመታች። ቻይናዊያን ተራቡ፤ ጎረቤት ሀገራትን ደጅ ጠኑ፤ ታላቁን ረሀብ መሻገር ያልቻሉ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቻይናዊያን በረሀብ አለቁ። በቻንግሻ የሚገኘው የማኦ ዘዶንግ ግዙፍ ሐውልት መራራ ጽዋን ተጎነጩ። የሀገሪቷ መሪ ማኦ ዘዶንግ በወቅቱ ፈተና ተስፋ ሳይቆርጥ ሀገር አሻጋሪ ፖሊሲውን ገቢራዊ አደረገ። ልመናን ለትውልድ ላለማውረስ፣ ንቅዘትን(ሙስናን) ነውር የሚያደርግ ስርዓት አጸና። ስራን ወንጌል፤ ሙስናን ወንጀል ያደረገ ጽኑ ስርዓተ መንግስት ገነባ። ከራሷ አልፋ ለዓለም የተረፈችዋን የዛሬዋን ቻይና በጽኑ መሰረት ላይ አነበረ። የዛሬዋ ቻይና ከዓለማችን ቁንጮ ልዕለ ሃያል ሀገራት አንዷ ናት። ከራሷ አልፋ ለዓለም ተርፋለች፤ የቻይና ቴክኖሎጂ ምጥቀትና ርቀት ዓለም ጉድ አሰኝቷል። በቅርቡ ሀገረ ቻይናን ከጎበኙ ጋዜጠኞች አንዷ ሆኜ ‘መልክዓ ቻይና’ን በወፍ በረር ቃኘሁ። በዚህ ማስታወሻዬ በቻይና የቴክኖሎጂ ልህቀትና ምጥቀት ላይ ብቻ አተኩራለሁ። ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ህዝብ ባላት፣ በ14 ሀገራት በምትዋሰነው፣ በአንድ ኮሚኒስት ፓርቲ በምትመራው ሀገር ቻይና በነበረኝ የ15 ቀናት ቆይታ ቻይና እንደ ጥንተ ታሪኳ ሁሉ በዘመኑ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ላይ ያላትን የመራቀቅ ጥግ ታዘብኩ። ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን የመቅደም እሽቅድድሟ ‘አጃይብ’ ያሰኛል። በሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና በማዕከላዊ ቻይዋ በምትገኘው የሁናን ግዛት ዋና ከተማ ቻንግሻ ምልከታዬ ቻይና ’ከተባለላት በላይ’ የቴክኖሎጂ ምጥቀቷ አስደንቆኛል። ምናልባትም የመጀመሪያ ጉዞዬ መሆኑም ነገሩን በአንክሮት እንድመለከት ሳያስገድደኝ አልቀረም። የሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከ22 ሚለዮን የሚልቅ ህዝብ በጉያዋ የታቀፈችው ታላቋ ቤጂንግ ከተማ ከዓለማችን ግንባር ቀደም የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህል፣ የቱሪዝምና የዲፕሎማሲ ማዕከላት አንዷ ናት። የአዲስ አበባ እህት ከተማ በዚህ ወቅት ሞቃታማ አየር ጸባት አላት። ቤጂንግ የ21ኛው ክፍል ዘመን የኪነ ህንፃና ክትመት ቴክኖሎጂ ያበበች ብቻ አይደለችም፤ ይልቁኑም በዛፎች ሀመልማላዊ ገጽታ የተላበሰች ውብ መዲና እንጂ። በሕንፃዎችም፣ በዛፎችም የተደነነች ከተማ። በተፈጥሮ የበቀሉ የሚመስሉ ሰማይ ታካኪ ሕንጻዎች፤ የመንገድ መሰረተ ልማት ስፋት፣ ጽዳትና ጥራት ‘ኩልል’ ያለች፣ ‘ምልል’ የምታደርግ ከተማ ያደርጋታል። ቤጂንግ ከተማ ከዘመናችን አስደናቂ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አንዱ በሆነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ) ሕይወትና ኑሮን እንዴት እንዳቃለለ የቤጂንግ የዕለት ከዕለት ክዋኔ ሁነኛ ማሳያ ነው። ቻይኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ተጠበዋል፤ መጠበብ ብቻም ሳይሆን ኑባሬያቸውን ሰው ሰራሽ አስተውሎት መር አድርገዋል። ከሮቦት መስተንግዶ እስከ ሰው ሰራሽ ፀሐይ መራቀቅ ይስተዋላል።   ካረፍኩበት ሆቴል (15ኛ ወለል ላይ ከሚገኘው መኝታ ክፍሌ) ሆኜ ያዘዝኩት ምግብ በቅጽበት አስተናጋጇ ‘ከች’ ብላ ትደውላለች። ፍጥነቷ ስትገረም፤ አስተናጋጆች ሮቦቶች መሆናቸውን ስትመለከት ይበልጥ ትደነቃለለህ። በክፍሌ ውስጥ ማብሪያ ማጥፊያ ስጫን መጋረጃው ሲከፈት መደንገጤን አልሸሽግም፣ ከምሽቱ 3 ሰዓት ፀሐይ አለመጥለቋን ስመለከት ‘የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ወጣች እንዴ?’ ማለቴ አልቀረም። በነገራችን ላይ የቻይና የሰው ሰራሽ ፀሐይ ሳይንሳዊ ፈጠራ ሁለት ግዜ ተሞክሮ ያለምንም እንከን እንደሚሰራ ነግረውናል። የሰው ሰራሽ ፀሐዩ ሃይድሮጅን እና ዱተሪየም ጋዞችን እንደ ሀይል ማመንጫ ነዳጅነት በመጠቀም ንጹህ ኢነርጂን ለማመንጨት ታስቦ ዲዛይን እንደተደረገና ሰው ሰራሽ ፀሐይ በርሐን ከተፈጥሮ ፀሐይ 13 እጥፍ ያክል ሙቀት እንደሚያመነጭም ሰምተን ተደንቀናል። የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ፕሮጀክት የሥራ ሰዓትን ከ13 ሰዓት ወደ 24 ሰዓት ለመጨመርና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብ የሰነቀ ነው። በቻይና በሰዉ ቅርፅ የተሰሩ ሮቦቶች በእግር ኳስ ጨዋታዎች ተወዳጅነት አትርፈዋል። ቤጂንግ የሚገኘው ሂዩማኖይድ የተሰኘ የሮቦት ቡድን የሰራቸው ሮቦቶች አመርቂ ውጤት ከራቀው የሀገሪቷ እግር ኳስ ቡድን ይልቅ የሀገሬውን ቀልብ እንደሳቡ ይነገራል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት በታገዘ የሮቦቶች ውድድር አያሌ ቻይናዊያን ይታደማሉ። ሮቦቶቹ በጨዋታ መሐል ቢወድቁ በራሳቸውን ይነሳሉ፤ ቢጎዱም ከሜዳ የሚወጡበት ስርዓት ተዘርግቷል። የታላቋ ቻይና ሰዎች ቴክኖሎጂን ከችግር መፍቻነት ወደ መዝናኛነትም አልቀውታል። በሀገራችን እንደ አዲስ ቴክኖሎጂ በንግዱ ስርዓት ውስጥ እየተዋወቀ ያለው የፈጣን ምላሽ መለያ ወይም ኪው አር ኮድ(Quick Response code) በቻይና ዕለታዊ ከዋኔዎች ቅንጦት አይደለም። በቻይና ማንኛውም ግልጋሎት በዚህ በዲጂታል ስርዓት ይከወናል። እንደሌሎች ስልጡን ሀገራት ሁሉ በንክኪ የሚደረግ ገንዘብ ዝውውር ቀርቷል። በቤጂንግ ጎዳናዎች በኪው አር ኮድ(QR Code) በሚንቀሳቀሱ ሞተር ሳይክሎችን በየመንገዱ ተሰድረዋል፤ የፈለገ መንገደኛ ሳይክሎችን በመጠቀም ወደ ፈለገበት ስፍራ ተንቀሳቅሶ ክፍያውን በኪው አር ኮድ ከፍሎ ይሄዳል። ሌላውም እንዲሁ። በአዲስ አበባ መኖሪያ ሰፈሬ የነበሩ ሳይክሎኝ ከደጃችን ደብዛቸው እንደጠፋ ሳስብ በቻይኖች ብልሃት፣ ታማኝነትና የከተሜነት ልህቀት ቀናሁ። በርግጥ በቻይና ኪው አር(QR) ኮድ ለተገለገልንበት መክፈያ ብቻ ሳይሆን ለልመናም መዋሉን ሲመለከቱ ፈገግ ሊሉ ይችላሉ። በቻይና ይህም አለ በማለት። በርግጥ በቤጂንግ የሰው እጅ ከሚያይ ይልቅ ጆሮቸውን ቢቆጥርጣቸው የሚሰሙ የማይመስሉ አዛውንቶች ሳይቀር በስራ ላይ ተጠምደው ይስተዋላሉ። ከቻይናውያን ጋር ለመግባባት በተለይም በንግድ ማዕከላት የቻይንኛ ቋንቋ መረዳት ግድ ይላል። “ሃው ማቺ፣ ጉዳ ጉዳ፤ ሺሼ፣ ኢ፣ አር…” እና መሰል ቃላት ማወቅ ይበጃል። ከዚህ ባለፈ በምልክት መግባባት አልያም በቋንቋ ተርጓሚ መተግበሪያ መጠቀም ያሻል። የቻይና ሰራሽ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምርቶች በራሳቸው ብራንድ፣ ቋንቋና መልክ እየተመረቱ በተመጣጣሽ ዋጋ ለህዝቦቿ ተደራሽ እየተደረጉ ነው። የቻይና የራስ-በቅነት ጥረት ያስቀናል። በቴክኖሎጂ፣ በባሕልና በኢኮኖሚ ተጽዕኖ ተላቀው በራሳቸው ለመቆም የሄዱበት ርቀት ግሩም ነው። ግብይቶች በራሳቸው ገንዘብ ብቻ ይከወናል። በወቅቱ ምንዛሬ አንድ የአሜሪካ ዶላር ሰባት የቻይና ገንዘብ(ዩዋን) ነው። ከምዕራባዊያን ማህበራዊ ትስስር ገጾች(ለምሳሌ ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክ) በሕግ በማገድ የራሳቸውን መተግበሪያ አበልጽገው ገቢራዊ አድርገዋል። ‘ዊቻት’ የተሰኘው መተግበሪያ ሁሉም ቻይናውያን መገልገያ ነው።   ከቤጂንግ ሌላ ያስደነቀችኝ ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከተማ ነች። ቻንግሻ ስመ-ብዙ ነች። ከሶስት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ ጠገቧ የሁናን ግዛት ርዕሰ መዲና ቻንግሻ ‘የከዋክብት ከተማ’ ትሰኛለች። በነገራችን ላይ ማኦ ዘዶንግ ትውልዱ ሁናን ግዛት ውስጥ ነው። ቻንግሻ በስራ ከተማነቷ ‘የማታንቀላፋው መዲና’ ትባላለች። በመዝናኛ ስፍራነቷ ‘የተዝናኖት መነሃሪያ’ የሚል ተቀጥላ ስም አላት። ‘የሚዲያ ጥበብ’ ስፍራም ትሰኛለች። በኢንዱስትሪ፣ በጥንታዊ ሐውልቶች፣ አብያተ መቅደሶች፣ ታሪካዊ ስፍራዎች መገኛ በመሆኗ በቱሪስቶች ተወዳጅ ከተማ ናት። ትናንትና ዛሬን ያዋደደች፣ ታሪክና ባህል ባዛነቀችዋ ቻንግሻ የአምስት ቀናት ቆይታዬ ብዙ ገጽታዋ አስደምሞኛል። የሻንግ ወንዝን ተንተርሳ፣ በተራራማ፣ በሜዳማና ኮረብታማ መልክዓ ምድር በማዛነቅ የተቆረቆረች በመሆኗ የስብት ማዕከል ሆናለች። እንደ ቤጂንግ በደን የተከበበች፣ በዘመነኛ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች እና በታሪካዊ ኪነ ሕንጻዎች የተጌጠች ከተማ ናት። ከዚህ ባሻገር የአምራች ኢንዱስትሪዎች መናገሻም ናት። የምቹ ከተሜነትና ጠንካራ የስራ ባህል በግላጭ የሚስተዋልባት ከተማ። የዓለማችን ገዙፉ በጣም ሞቃታማ አየር ጸባይ ባላት ቻንግሻ ሌት ከቀን ይሰራል። ፋብሪካዎቿ አይተኙም። ሌትና ቀኑ የሚታወቀው በሰዓት ብቻ እንጂ የስራና የንግድ ድባቡ እኩል ነው። ብርሃናማዋ ቻንግሻ ‘የቻይዊያን መስቀል’ በተሰኘው በቀይ በተቀለመው መስቀልም ትታወቃለች። በርግጥ ከዓለማችን ግዙፍ ማማዎች አንዱ የሆነው ሕንጻም መገኛ ናች። በጥቅሉ የቻይና ጉብኝት ትዝብቴ የገናና ታሪክ ባለቤቷ ሀገር ከባድ ውጣ ውረዶችን አልፋ ዛሬ ዓለምን እየቀደመች መሆኑን ሳስብ፤ እንደቻይና ሁሉ የሺ ዘመናት ገናና ታሪክና አኩሪ ገድል ያላት ኢትዮጵያስ የሚል ተጠየቅ እንዳውጠነጥን አድርጎኛል። ቻይናዊያን የዘመን የፈተና ቋጠሮዎቻቸውን ፈታተው ከዛሬ ከፍታ ሰገነት ላይ ወጥተዋል። ከዛሬም በበለጠ ነገን በጽኑ መሰረት ላይ እየገነቡ ነው። እኛስ? ብዬ ሳስብ በቁጭትና በተስፋ ተዋጥኩ! ሰላም!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም