ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የስንዴ ልማቱ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ለተያዘው  ትልም መሳካት ትልቅ  ማሳያ ነው - የአመራር አባላት
Dec 8, 2025 30
ወላይታ፤ ሕዳር 29/2018 (ኢዜአ)፦ እየተከናወነ የሚገኘው የስንዴ ልማት የምግብ ዋስትናን በአጠረ ጊዜ ማረጋገጥ እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ መሆኑን በወላይታ ዞን ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ መካከለኛና ከፍተኛ አመራር አባላት ተናገሩ። "በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ በዞኑ ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ መካከለኛና ከፍተኛ አመራር አባላት በቦዲቲ ከተማ እና በዳሞት ጋሌ ወረዳ የስንዴ ልማት፣ የኢንዱስትሪ፣ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የአመራር አባላቱ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት፤ እየተከናወኑ የሚገኙ የስንዴ ልማት ስራዎች የምግብ ዋስትናን በአጠረ ጊዜ ማረጋገጥ እንደሚቻል ማሳያ ነው። አስተያየታቸውን ከሰጡ የአመራር አባላት መካከል ወይዘሮ መሰረት ሆጃሞ ስልጠናው ከመናገር በላይ ሰርተን ለመለወጥ የሚያስችል መስፈንጠሪያ አቅምን አግኝተንበታል ብለዋል። በሁሉም ዘርፎች እየመጡ ያሉ ውጤቶች የሚያስደስቱ መሆናቸውንና በስንዴ ልማቱ የተመዘገበው ስኬት በምግብ ሰብል ራስን ለመቻልና ከተመጽዋችነት ለመውጣት የተያዘው ውጥን እንደሚሳካ ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም በስልጠናውም ሆነ በጉብኝቱ ያገኙትን አቅም በማቀናጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት ለመስራት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ስልጠናው አመራሩ ሀገሩን አውቆ አቅሙን እንዲያወጣ ያግዛል ያሉት ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ አንዱዓለም ጌታሁን በወረዳው ያዩት ልማት ለሀገር ትልቅ ተስፋ ነው ብለዋል። በወረዳው አርሶ አደሩ በክላስተር በመደራጀት እያለማ የሚገኘው የስንዴ ልማት ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ የወላይታ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አማረ አቦታ (ዶ/ር) በዞኑ በግብርናው፣ በኢንዱስትሪው፣ በከተማ ልማትና በቱሪዝም እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ስልጠናውም በአመራሩ ዘንድ ቁጭት በመፍጠር የህዝቡን መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ተግቶ እንዲሰራ አቅም የሚፈጥር እንደሆነም ገልፀዋል። ያሉ ፀጋዎችን አሟጦ በመጠቀም የግብርናን ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ከዚህ ቀደም ምርት የማይሰጡ ማሳዎችን በኖራ በማከም፣ በመስመር በመዝራትና ግብዓት በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን የመጨመር ስራ መሰራቱንም አስረድተዋል። ሰልጣኝ አመራር አባላቱ ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ተግዳሮቶችን ወደ ዕድል በመቀየር በየአካባቢው ያሉ እምቅ ፀጋዎችን በማልማት በሁሉም ዘርፎች እመርታ ለማስመዝገብ መትጋት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።  
ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ይካሄዳል-ኢንስቲትዩቱ
Dec 8, 2025 85
አዳማ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ )፡- ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የክትባት ዘመቻውን ለማሳካት ያለመ የባለድርሻ አካላት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።   በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች ቅኝትና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክተር አቶ እንዳለ ዘመነ እንደገለጹት፤ ፖሊዮን ለማጥፋት የተቀናጀ ሀገር አቀፍ ክትባት ዘመቻ በመላው ሀገሪቱ ይካሄዳል። ዘመቻውን ስኬታማ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የክትባት ዘመቻው 25 ሚሊዮን የሚሆኑ ሕፃናት ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በሁሉም ክልሎች የክትባቱ ቁሳቁስና ተያያዥ ግብዓት አቅርቦት በየወረዳዎቹ የጤና ተቋማት ደርሰው ወደ ቀበሌዎች እየተሰራጩ እንደሚገኙ አንስተው፤ የሰው ሃይል ዝግጅትን ጨምሮ የሕብረተሰብ ንቅናቄ መካሄዱንም አክለዋል።   በዘመቻው የቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት ከመስጠት ጎን ለጎን የበሽታው ምልክት ያሳዩትን ሕፃናት የመለየት ስራ እንደሚከናወን አስረድተዋል። በጤና ሚኒስቴር የክትባት ፕሮግራም የኮሙኒኬሽን አማካሪ ወይዘሮ ፀጋነሽ ገድሉ እንዳመለከቱት፤ በዘመቻው መደበኛ የፖሊዮ ክትባት ያልወሰዱ ሕፃናት ይካተቱበታል። በጊዜያዊ የክትባት ጣቢያዎችና ወደ ጤና ተቋማት ሄደው ክትባቱን እንዲወስዱ የማድረግ ስራ ይሰራል ነው ያሉት ።   ክትባቱ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ከተሞች፤ ወረዳዎችና ቀበሌዎች በተመሳሳይ ወቅት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ ለስኬታማነቱም በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ትብብርና ዕገዛ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል ።  
የብረታ ብረት ኢንዱስትሪው እያመጣ ያለው ለውጥ የገጠርና የከተማ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ የሚያግዝ ነው
Dec 8, 2025 53
ባሕርዳር፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የብረታ ብረት ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያመጣ ያለው ለውጥ የተጀመረውን የገጠርና የከተማ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ የሚያግዝ መሆኑ ተገለጸ። በክልሉ ያሉ የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት አመራሮችና ባለሙያዏች የመንግስት የልማት ድርጅት የሆነውን የአማራ ብረታ ብረት ኢንዱስትሪና ማሽን ቴክኖሎጅ ኢንተርፕራይዝን ዛሬ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ዓላማውም የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት አመራሩና ባለሙያው በዘርፉ የገበያ ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ ያለውን ተግባር በማገዝ ሚናቸውን እንዲወጡ ለማነሳሳት እንደሆነ ተነግሯል።   በዚህ ወቅት የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ አባይ መንግስቴ እንዳሉት፤ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን አቅም በማሳደግ እድገቱን ለማፋጠን እየተሰራ ይገኛል። በተለይም የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት ለማሳደግና ከተሞችን ለማዘመን ቴክኖሎጂ ላይ መስራት መጠየቁን አስረድተዋል። ይህንን ለማሳካት የብረታ ብረት ኢንዱስትሪው ዘርፍ እየመጣ ያለውን ለውጥ የገጠርና የከተማ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ገልጸዋል። በዚህም የአማራ ብረታ ብረትና ማሽን ቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ የኢንዱስትሪ መለዋወጫዎችን፣ አነስተኛ ማሽኖችን፣ ስማርት ፖሎችንና ሌሎች ግብአት እያመረተ መሆኑን አስረድተዋል። የኢንተርፕራይዙ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘላለም በላይ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢንተርፕራይዙ የአምራች ኢንዱስትሪውን ችግር ለማቃለል እየሰራ ይገኛል። ለአብነትም የፋብሪካዎችን መለዋዎጫዎች በማምረት የኢንዱስትሪውን ዘርፉ እያሳደገ መሆኑን አንስተዋል። ከውጭ የሚገቡ የኢንዱስትሪና ፋብሪካዎች ግብአት አምርቶ በማቅረብ የክልሉን ብሎም የሀገሪቱን እድገት ለማፋጠን ኢንተርፕራይዙ የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።   ኢንተርፕራይዙ ከሚያመርታቸው ውስጥ ትራንስፎርመር፣ ማረሻ፣ ተንጠልጣይ ድልድይ እና ስማርት ፖል እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። ቴክኖሎጅን የማላመድ፣ የመፍጠርና የማበዛት ስራ በማከናወን የውጭ ምንዛሬን ለማዳን ትኩረት መስጠቱን አመልክተዋል። በቀጣይ የውሃ ፓንፕ፣ የመኖ ማቀነባበሪያ፣ አነስተኛ ትራክተር፣ የበቆሎ መፈልፈያና ሌሎች ማሽነሪዎችን ለማምረት አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱንም ጠቁመዋል። ኢንተርፕራይዙ ለ600 ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉንም አንስተዋል።
የልማት ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንሰራለን
Dec 8, 2025 52
ቦንጋ ፤ ሕዳር 29/2018 (ኢዜአ)፡-የልማት ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁጭት እንደሚሰሩ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አመራሮች ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ማጠቃለያ ላይ አመራሩ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት በመፍጠን፣ በመፍጠር፣ በማባዛትና በማጥራት መስራት እንዳለበት መመሪያ መስጠታቸው ይታወሳል። በስልጠናው ኢዜአ ያነጋገራቸው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አመራሮችም ስልጠናው በየአካባቢው ያሉ የልማት ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅም እንደሆናቸው ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የካፋ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ሀብታሙ ገብረስላሴ እንደገለጹት በክልሉ ያሉ የተፈጥሮ ሀብቶችን አልምቶ ለኢንቨስትመንት ለማዋል ከምንጊዜውም በላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ገልጸዋል። በቀጣይ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ፈጠራና ፍጥነት በማከል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በስልጠናው ያገኙትን አቅም ወደተግባር እንደሚቀይሩ አረጋግጠዋል። በዞኑ ኢንቨስትመንትን በመሳብ የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ለማሳደግና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁጭት ይሰራል ሲሉም ገልጸዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ የዞኑ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ አዱኛ አዴሎ፣ በእጃችን ያለውን ሀብት ማየትና ማልማት ባለመቻላችን ብዙ ነገር እንዳጣን ስልጠናው አሳይቶናል ብለዋል። ከዚህ ችግር በመውጣት ከአካባቢው ሀብት የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ ማልማት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብና ለውጥ የታየባቸውንም ለማስቀጠል የሚችል የሰው ሀይል መፍጠር ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል። ስልጠናው በፈጠራና በፍጥነት እንዴት ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚቻል አቅም የገነቡበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ የካፋ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ንጉሴ ባዩ ናቸው። በተጨማሪም በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ እንዴት ማልማት እንደሚቻልና ውጤታማነትን በማስቀጠል የህዝብንተጠቃሚነት ለማሳደግ ዕውቀት ማግኘታቸውንም ተናግረዋል። ይህን መነሻ በማድረግም በቀጣይም በግብርና፣ በከተማ ልማት፣ በቱሪዝምና በሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት እምርታዊ ለውጥ ለማምጣት በቁጭት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
የሚታይ
ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ይካሄዳል-ኢንስቲትዩቱ
Dec 8, 2025 85
አዳማ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ )፡- ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የክትባት ዘመቻውን ለማሳካት ያለመ የባለድርሻ አካላት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።   በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች ቅኝትና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክተር አቶ እንዳለ ዘመነ እንደገለጹት፤ ፖሊዮን ለማጥፋት የተቀናጀ ሀገር አቀፍ ክትባት ዘመቻ በመላው ሀገሪቱ ይካሄዳል። ዘመቻውን ስኬታማ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የክትባት ዘመቻው 25 ሚሊዮን የሚሆኑ ሕፃናት ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በሁሉም ክልሎች የክትባቱ ቁሳቁስና ተያያዥ ግብዓት አቅርቦት በየወረዳዎቹ የጤና ተቋማት ደርሰው ወደ ቀበሌዎች እየተሰራጩ እንደሚገኙ አንስተው፤ የሰው ሃይል ዝግጅትን ጨምሮ የሕብረተሰብ ንቅናቄ መካሄዱንም አክለዋል።   በዘመቻው የቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት ከመስጠት ጎን ለጎን የበሽታው ምልክት ያሳዩትን ሕፃናት የመለየት ስራ እንደሚከናወን አስረድተዋል። በጤና ሚኒስቴር የክትባት ፕሮግራም የኮሙኒኬሽን አማካሪ ወይዘሮ ፀጋነሽ ገድሉ እንዳመለከቱት፤ በዘመቻው መደበኛ የፖሊዮ ክትባት ያልወሰዱ ሕፃናት ይካተቱበታል። በጊዜያዊ የክትባት ጣቢያዎችና ወደ ጤና ተቋማት ሄደው ክትባቱን እንዲወስዱ የማድረግ ስራ ይሰራል ነው ያሉት ።   ክትባቱ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ከተሞች፤ ወረዳዎችና ቀበሌዎች በተመሳሳይ ወቅት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ ለስኬታማነቱም በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ትብብርና ዕገዛ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል ።  
የመደመር መንግሥት እይታ በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር ፈጥሯል
Dec 8, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት እይታ በኦሮሚያ ክልል ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር መፍጠሩን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። የዓለም ቱሪዝም ቀን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ለ21ኛጊዜ “ቱሪዝምና ዘላቂ ለውጥ” በሚል መሪ ሃሳብ በክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አዘጋጅነት በምሥራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ከተማ ተከብሯል።   የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን ታምሩ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሀብቶች ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ተደርጓል። የመደመር መንግሥት እይታ በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሃብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር መፍጠሩን ገልጸው፤በክልሉ ያሉ ሁሉም ወረዳዎች የራሳቸው የቱሪዝም መዳረሻ እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት። የምስራቅ ባሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጃርሶ ቦሩና በበኩላቸው ዞኑ በርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ሃብቶች እንዳሉት ተናግረዋል።   ለአብነትም የሶፍ ዑመር ዋሻ፣ ድሬ ሼህ ሁሴን፣ አስደናቂ መልክዓ ምድሮች እና ጥቅጥቅ አረንጓዴ አካባቢዎች እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። ከዚህ ቀደም በአካባቢው የሚገኙትን ሃብቶች በማልማት ረገድ ምንም እንዳልተሰራ አንስተው፤ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በፌዴራልና በክልሉ መንግሥት ሰፋፊ መሠረተ ልማቶች በትኩረት እየተገነቡ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ የመንገድ፣ የመብራት፣ የቴሌኮም ኔትወርክን ጨምሮ ቱሪዝምን የሚያነቃቁ መሠረተ ልማቶች በመገንባታቸው ዞኑ ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆን መቻሉን ተናግረዋል። መሠረተ ልማቶቹ በዞኑ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ ማገዛቸውን አስታውቀዋል።  
የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ልማት ለሰላማዊ አገልግሎት ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል ነው 
Dec 8, 2025 106
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ልማት መርሃ ግብር ለሰላማዊ አገልግሎት ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል መሆኑን የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ ገለጹ። የኢትዮጵያን የኒውክሌር ኃይል ልማት መርሃ ግብር ማስጀመሪያና የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን ሥራ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረክ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ፣ የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሚካኤል ቹዳኮቭና የባለድርሻ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ ፤ የኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ልማት የኃይል ደህንነትን በማረጋገጥ የኢኮኖሚያዊ ሽግግርና የረጅም ጊዜ የመቋቋም አቅም ግንባታ ላይ የተመሠረተ ብሔራዊ የልማት ተነሳሽነት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ንጹህ የኃይል አቅርቦት የማመንጨት አቅምን በማላቅ በጤና፣ ግብርና፤ በኢንዱስትሪ እና የምርምር ትግበራ ማዕቀፍ የተቃኘ መሆኑን ገልጸዋል። የሰላማዊ አማራጭ የኒውክሌር ሳይንስ ልማት መርሃ ግብሩ ዓላማ የኢትዮጵያዊያንን ህይወት በተጨባጭ የሚያሻሽሉ ጥቅሞችን የሚያስገኝ ዕድል ማረጋገጥ እንደሆነም ተናግረዋል።   የኃይል አቅርቦት የዕድገት ሞተር ነው ያሉት ኮሚሽነሩ የሰላማዊ አማራጭ አስተማማኝ የኒውክሌር ኃይል ልማት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን ዕድገት ጥራትና ፍጥነት ይቀርፃል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የኒውክሌር ኃይል ልማት ቁርጠኝነት ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ ታሳቢ ያደረገ ደፋር ውሳኔ መሆኑን አብራርተዋል። በ​ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ በጉባ ከተበሰሩ ማግስት በሩሲያ የተካሄደው ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል መድረክ ድረስ ኢትዮጵያ ለሰላማዊ የኒውክሌር ልማት ያላትን ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን አስታውሰዋል። በዚህም ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ አገልግሎት ብቻ ለመጠቀም ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነች ብለዋል። ​የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን በተሰጠው ግልጽ ሥልጣንና ጠንካራ መዋቅር ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። ​የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር የተፈጠረው የሥልጠና ፕሮግራምና የባለሙያ የልምድ ልውውጥ፣ ክህሎት ግንባታና የቴክኒክ ትብብር እየተሳለጠ መሆኑን ተናግረዋል። ​በቀጣይም ኢትዮጵያ በዕውቀትና በሰላማዊ የኒውክሌር ልማት የጋራ ርዕይ በመመስረት ከዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር የትብብር ስራን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ልማት መርኃ ግብር ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ማዕቀፎች ጋር በማጣጣም የሚተገበር ነው 
Dec 8, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ልማት መርኃ ግብር ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ማዕቀፎች ጋር በማጣጣም የሚተገበር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያን የኒውክሌር ኃይል ልማት መርኃ ግብር ማስጀመሪያና የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን ሥራ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የሰው ልጆች ስልጣኔ ከእሳት፣ ውኃ፣ ነፋስና እንፋሎት የኃይል አማራጭ ልማት ጋር የተቆራኘ ነው። የኃይል አቅርቦት የቴክኖሎጂ ግኝቶች ከኢኮኖሚ ልማት ጋር የተቆራኘ አስተማማኝና ተመጣጣኝ የማኅበረሰብ ዕድገት ለመፍጠር አቅም እንዳላቸው ገልጸዋል። ​ ኢትዮጵያም በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ቴክኖሎጂ ልማት በአዲስና አስፈላጊ የኢንዱስትሪ አብዮት ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ተናግረዋል። ​የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ልማት በአስተማማኝ፣ የረጅም ጊዜና ንጹህ የኃይል ምንጭነት ከፍተኛ ትኩረት እያገኘ መምጣቱን አንስተዋል። የኒውክሌር ኃይል ለዘላቂ ብልጽግና መሠረት ነው ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገትና ብዙ የሕዝብ ቁጥር የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የረጅም ጊዜና ስትራቴጂካዊ የመሠረ ልማት ግንባታ ኢንቨስትመንቶችን ማስፋት አስፈላጊ ሆኗል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል ልማት መርኃ ግብር በጤና፣ በግብርና እና በሌሎች የልማት መስኮች ትግበራ የኃይል ፍላጎትን በማሟላት ብልጽግናን የማረጋገጥ ትልም ያነገበ መሆኑን አስገንዝበዋል። ​ የሰላማዊ ኒውክሌር ልማት መርሃ ግብርም የምንፈልጋትን ኢትዮጵያ እውን የሚያደርግ ብሔራዊ የልማት ፕሮጀክት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ ዳታ ማዕከላት፣ ባቡሮችና ተሸከርካሪዎች እንደ ኒውክሌር ኃይል ባሉ ከታዳሽና አስተማማኝ የኃይል ምንጮች በሚገኝ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩባት ሀገር የማድረግ ጉዞም በወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋርም የኢትዮጵያን ብሔራዊ የኒውክሌር ልማት መርሃ ግብር የደህንነትና ግልጽነት ደረጃ ለማስጠበቅ እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ልማት ውጥኗን ከጀመረች ማግስት አንስቶም የዓለም አቀፍ በአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ እየሰጠ ለሚገኘው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ልማት መርሃ ግብር ጠንካራ ትብብር ላይ በመመስረት ከዓለም አቀፍ መስፈርቶች፣ ደረጃዎችና የዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ማዕቀፎች ጋር ሙሉ በሙሉ በማጣጣም የሚተገበር መሆኑንም ተናግረዋል። የአፍሪካ ኩራት የኢትዮጵያ የአቬሽን ኢንዱስትሪ እና የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬትም በሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል አማራጭ ያላትን የብልጽግና ተምሳሌት ሕልም ለማሳካት እንደሚሰራ ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ፣ የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሚካኤል ቹዳኮቭና የባለድርሻ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በውጭ በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ተከበረ
Dec 8, 2025 96
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች ተከብሯል። በዓሉ የተከበረው "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ነው። በአከባበሩ ላይ የሚሲዮን መሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና ሰራተኞች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የማህበረሰብ ተወካዮችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ኢትዮጵያ የብዝኃነት ተምሳሌት እና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ባሳየ መልኩ ተከብሯል። የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦችና አልባሳት ለእይታ የቀረቡ ሲሆን የብሔሮች ብሔረሰቦች ሙዚቃዎችና ባሕላዊ ውዝዋዜዎች የሚገልጹ ሁነቶችም ቀርበዋል። በዓሉ በቻይና፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ቱርኪዬ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኳታር፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቤልጂየም፣ ፓኪስታን፣ ኮትዲቭዋር፣ ስዊድን፣ ኮሪያ ሪፐብሊክ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ አውስትራሊያ፣ ዩጋንዳ፣ ሩዋንዳ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ ቀኑ ከተከበረባቸው ሀገራት መካከል ይገኙበታል። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ዛሬ ተከብሯል።
ብልጽግና ፓርቲ ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ
Dec 8, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ብልጽግና ፓርቲ ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ፓርቲው ያስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡- እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አደረሰን አደረሳችሁ! የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በየደረጃውና በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር ቆይቶ በዛሬው ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በደማቅ የማጠቃለያ መርሀግብር እየተገባደደ ይገኛል፡፡ የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ከህዳር 01 ጀምሮ ለተከታታይ አንድ ወር በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በደማቅ ኩነት እንዲከበር ተደርጓል፡፡ ይህም እውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት እና ፌዴራላዊ ሥርዓት ለመገንባት የተያዘው ቁርጠኝነት ማሳያ ነው፡፡   ብልፅግና ፓርቲና የመደመር መንግሥት 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ከዕለታዊ ክብረበዓል በላይ የአጀንዳው ትክክለኛ አስፈላጊነት በውል በመረዳት በበዓሉ ስያሜ የተገለጹትን የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የፍትህ፣ የእኩልነት፣ የልማትና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች በተግባር በመመለስ መሆን አለበት ብሎ ያምናል፡፡ ለዚህም በዓሉ በአንድ ቀን ከማክበር አንድ ወር ሙሉ በመውሰድ በየክልሉና ከተማ አስተዳደሩ ያሉት ባህሎችና ነባራዊ እውነታዎች ታሳቢ በማድረግ በተከታታይ እንዲከበር መደረጉ የዚህ እምነት አንዱ ማሳያ ነው፡፡ በዓሉ “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል እንዲከበር የተመረጠበት ምክንያት እውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት እና ፌዴራላዊ ሥርዓት የሚገነባው ዴሞክራሲያዊ መግባባት በመፍጠር መሆኑ በግልጽ አመላክቷል፡፡ ዴሞክራሲያዊ መግባባት ወይም የመግባባት ዴሞክራሲ የሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት ከሆኑ ዕሳቤዎችና ተግባራት አንዱ ሲሆን የሀገራችን የዘመናት ችግር እና የሥርዓት ስብራት ሆኖ የቆየውን የዴሞክራሲ ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ እየተተገበረ ያለ ዕሳቤ ነው፡፡ ዋነኛው የኢትዮጵያ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ጥያቄ የዴሞክራሲ ጥያቄ ነበረ፡፡ ከለውጡ በፊት በነበሩት ዓመታት ይህንን በዓል የዕሳቤ ጥራት እና የተግባር ቁርጠኝነት ያልተፈጠረበት የይስሙላ የአደባባይ ትዕይንት ሆኖ ሲከበር ቆይቷል፡፡ ሙሉ ዕይታን መለያው ያደረገው ብልፅግና ፓርቲ ይህንን የዕይታና የተግባር ክፍተት በማረቅ የጎደሉትን የእውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት፣ ፌዴራላዊ ሥርዓት እና ዴሞክራሲያዊ መግባባት አላባውያን በማገናኘት ወደ ተቃና የለወጥና የዝላይ ምዕራፍ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ዴሞክራሲያዊ መግባባት የተዋንያን በተለይ ደግሞ የህዝብ ይሁንታና ተሳትፎ የሚያስተናግድ ዕሳቤና ማህበራዊ ውል ነው፡፡ የዴሞክራሲያዊ መግባባት አንዱና ዋነኛ መገለጫ ምርጫ ሲሆን የዘንድሮው የህዳር 29 በዓል ከ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ጋር ተያይዞ የሚታይ ነው፡፡ ያለፈው 6ኛ ሀገራዊ ምርጫ ለዴሞክራሲያዊ መግባባት መሠረት የጣለ ስኬታማ ምርጫ እንደነበረው ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ደግሞ የዚህ ዕሳቤና ማህበራዊ ውል የአፈጻጸም ከፍታ የሚታይበት እንዲሆን አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡ በዓሉ በያዝነው ዓመት ሲከበር የኢትዮጵያ ብልፅግና አይቀሬ ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ ፕሮጀክት መሆኑ በአያሌ ማሳያዎች የተረጋገጠበት በመሆኑ በዓሉ ይበልጥ ደማቅ አድርጎታል፡፡ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ መመረቅ ብልፅግና ፓርቲ ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር እንደሚፈጸም ማሳያ ነው፡፡ በዕለቱ የተበሰሩ 7ቱ በጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች ሆነው የዚህ ተግባር ቀጣይነት በማሳየት በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ መተማመንና ቅቡልነት ለመፍጠር ተችሎበታል፡፡ ይህ በመፍጠን፣ መፍጠርና ዝላይ የታጀበ አስደናቂ የልማት አርበኝነት የባህር በር አጀንዳችን ላይ ለመድገም ስንቅ በመሆን “ከግድቡ ወደ ባህሩ” በሚል ህዝባዊ መፈክር ከታሪካችንና ከማንነታችን አለአግባብ የተወሰደብንን የባህር በር ጥያቄያችን በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለማስመለስ እንደ ህዝብና ሀገር አንድ ሆነን እየሰራንበት እንገኛለን፡፡ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ስናከብር የመደመር መንግሥት ያስቀመጣቸውን አሻጋሪና ተስተካካይ ዕቅዶች እየተተገበሩና ውጤት እያመጡ መሆናቸውና ለዚህም ህዝብ በባለቤትነት የሚሳተፍበትና ተጠቃሚ እየሆነበት ያለ መሆኑ በመገንዘብ ነው፡፡ በቀጣይ ዓመት 21ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የምናከብረውም በአንድ እጃችን የጀመርናቸው የፀጥታና የልማት ሥራዎች አሳክተን በሌላው እጃችን ደግሞ ህዝቦች ለዘመናት የታገሉለትን የዴሞክራሲ ሥርአት ወደ ላቀ ደረጃ አድርሰን ነው፡፡ በጉጉት የሚጠበቀውና ነጻ፣ ፍትሀዊና አሳታፊ በመሆን የዴሞክራሲ እመርታ እንዲፈጠርበት በሚጠበቀው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች እንደ ከዚህ ቀደሙ በባለቤትነትና በላቀ ተነሳሽነት በመሳተፍ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሀገራችን ፀጥታ፣ ልማትና ዴሞክራሲ የሚጎመዝዛቸው ባዳዎችና ባንዳዎች ሀገር አፍራሽ እንቅስቃሴዎቻቸውን በንቃት በመከታተልና በመመከት እንዲሁም በዛሬው ቀን በድምቀት እያጠቃለልነው ያለነው በዓል መሪ ቃል የሆነውን “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” ተግባራዊ ለማድረግ ዴሞክራሲያዊ መግባባታችንን እና ህብረብሄራዊ አንድነታችንን በማጽናት መሆን አለበት፡፡ መልካም 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል! ብልፅግና ፓርቲ ህዳር 29፤ 2018 ዓ.ም
ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Dec 8, 2025 96
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል መንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፣ የክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች በበዓሉ ላይ ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአባቶቻችን ደም የወረስነውን ነጻነት በብልጽግና ማጽናት ከትውልዱ የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬ ላይ ከተሞች እያደጉ የገጠር መንደሮች ለመሻገር በትጋት እየሰሩ ያሉበት ወቅት መሆኑን ገልጸው፤ ታሪካዊ ቅርሶችም አቧራቸውን አራግፈው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ኩራት መሆናቸውን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ክረምት ከበጋ በማረስ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች መሆኑን ገልጸው፤ የወረስነውን ነጻነት ብቻ ሳይሆን የተሸከምነውን የትውልድ አደራ ማሰብ ይኖርብናል ብለዋል። ብልጽግናን ማሳካት ፈታኝ ሂደት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ማየት እንደሚገባ ተናግረዋል።   ትውልዱ ኢትዮጵያ ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ፈልፍሎ የማየት እና የማውጣት አቅም እንዳለው በጅምር ስራዎች መታየቱን አንስተዋል። በትብብር መንፈስ በብዙ ትጋት እና ልፋት አዲስ የታሪክ ገጽ መክፈት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ብልጽግና ምሉዕነት የሚረጋገጠው ኢትዮጵያውያን በህብረት መትጋት እና መስራት ሲችሉ መሆኑን አመልክተዋል። መተባበርን፣ መከባበርን እና በጋራ መቆምን እንዲሁም ብሔራዊ ጥቅምን የሁላችን ሀብት እና ስንቅ ማድረግ አለብን ብለዋል። የሀገርን መሻት እና የባዳን ክፋት መለየት እንደሚገባ ገልጸው፤ ኢትዮጵያውያን የባዳ ፍላጎት መሳሪያ መሆን እንደሌለባቸው ጠቁመዋል። የሀገርን ጥቅምና የህዝብ ክብር ማስቀደም እንደሚገባ ገልጸው፤ ለዘመናዊነት እና ለውጥ ክፍት መሆን እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ብዙ ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ አስደናቂ ውጤት በማስመዝገብ እያንሰራራች ትገኛለች ብለዋል። ይህን መልካም ጅማሮ ለማደናቀፍ ሙከራዎች መኖራቸውን ገልጸው፤ ማንኛውም ፈተና፣ ትንኮሳ እና ክፉ ሀሳብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ማቆም አይችልም ብለዋል።
መንግስት ሁለንተናዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ  ብዝኃነትን ከአንድነት ጋር የሚያስማማ መንገድ መርጦ በትኩረት እየሰራ ነው 
Dec 8, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት ሁለንተናዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ብዝኃነትን ከአንድነት ጋር የሚያስማማ መንገድ መርጦ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት "ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሐሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል፡፡   የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ብዝኃ ማንነት፣ ቋንቋ እና ባህል የሚገለጽበት ይህ በዓል በርካታ ዓላማዎችን አንግቦ እየተከበረ ይገኛል ብለዋል፡፡ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እርስ በእርሳቸው እንዲተዋወቁ፣ ባህላቸውንና ልምዶቻቸውን እንዲለዋወጡ ብሎም ህብረ-ብሔራዊ አንድነታቸውን ማጠናከር ማስቻሉን ገልጸዋል። የዘንድሮው በዓል ከቀደሙት የሚለየው "ዳግማዊ ዓድዋ" የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተመረቀበት እና የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች ጅማሮ በተበሰረበት ማግስት መከበሩ መሆኑንም አንስተዋል። በህብረ ብሔራዊ አንድነት የደመቀ ብዝኃነታችንን ለዓለም ገልጸን የምናሳይበት ቀን ነው ያሉት አፈ-ጉባኤው፤ እውነተኛ የፌዴራል ሥርዓት በመገንባት ሂደት አዲስ የታሪክ እጥፋት ላይ መሆናችንን የምናስገነዝብበት ነው ብለዋል፡፡   ለብዝኃነት ክብር የሚሰጥ የጋራ ማንነት እንዲኖር መስራት ይገባል ያሉት አቶ አገኘሁ፤ የጋራ ማንነትን ለማጽናትና በብሔራዊነት ላይ የተመሰረተ አሰባሳቢ ትርክት መገንባት እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ መንግስት ሁለንተናዊ ብልጽግናንን እውን ለማድረግ እና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ብዝኃነትን ከአንድነት ጋር የሚያስማማ መንገድ መርጦ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ይህንን እውን ከማድረግ አኳያም የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡
የበዓሉ መከበር የጋራ ትርክትን ለመገንባት እየተደረገ ያለውን የሀገራዊ ምክክር ሂደት ፍሬያማ ያደርገዋል- እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Dec 8, 2025 90
ሆሳዕና፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል መከበር የጋራ ትርክትን ለመገንባት እየተደረገ ያለውን የሀገራዊ ምክክር ሂደት ፍሬያማ እንደሚያደርገው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በሆሳዕና ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡   በበዓሉ ላይም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ የበዓሉ መከበር የጋራ ትርክትን ለመገንባት እየተደረገ ያለውን የሀገራዊ ምክክር ሂደት ፍሬያማ ያደርገዋል። በዓሉ የዳበረ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር የሀገረ መንግሥት ግንባታን በማጠናከር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል፡፡ በዓሉ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ባህላዊ ትውፊቶቻቸውን ከመለዋወጥ በተጨማሪ የእርስ በእርስ ትስስርን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል፡፡   በዓሉ የዘመናት ቁጭት ሆኖ የቆየውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በማጠናቀቅ ሌሎች አዳዲስ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ማግስት መከበሩ የተለየ ያደርገዋል ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የክልሉ ህዝብ ከሌሎች ህዝቦች ጋር በአብሮነት በመኖር የሚታወቅ ህዝብ መሆኑን ጠቅሰው ክልሉ ያለውን እምቅ አቅም በአግባቡ በመጠቀም ለሀገር ህልውና መጠበቅ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል፡፡ በተያያዘም 21ኛው የብሄሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ እንደሚዘጋጅ የተጠቆመ ሲሆን በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር እና በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ መካከል የሰንደቅ ዓላማ ርክክብ ተካሄዷል፡፡   በተመሳሳይም በበዓሉ አከባበር ስነ-ስርዓት ላይ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅን ተከትሎ የዋንጫ ርክክብ ስነ- ስርዓት ተካሄዷል፡፡ የዋንጫ ርክክቡን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) ለኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር አስረክበዋል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዓሉ የህዝቦችን ህብረብሔራዊ አንድነትና አብሮ የመኖር እሴት በማጠናከር በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል 
Dec 8, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፡- ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዓሉ የህዝቦችን ህብረብሔራዊ አንድነትና አብሮ የመኖር እሴት በማጠናከር ዘላቂ ልማትና ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ሃሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል።   በበዓሉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፤ ምክር ቤቱ የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን እንዲከበር ሲወስን ብሔር ብሔረሰቦች አርስ በእርሳቸው እንዲተዋወቁ፤ ባህላዊ እሴቶቻቸውንና መልካም ልምድና ተሞክሮዋቻቸውን እንዲለዋወጡና ህብረብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዘላቂ ሰላም ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለልማት በጋራ እንዲቆሙ ማድረግም እንዲሁ፡፡ ባለፉት 19 ዓመታት በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በተለያዩ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አስተናጋጅነት በዓሉ ሲከበር መቆየቱን ያስታወሱት አፈጉባዔው ይህም በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቦችን ህብረብሔራዊ አንድነትና አብሮ የመኖር እሴት በማጠናከር የሀገረ መንግስት ግንባታውን እና ዘላቂ ልማትና ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉንም አውስተዋል፡፡ የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የጋራ ትርክት ውጤት የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተጠነቀቀበት ወቀት የሚከበር መሆኑና የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞን እውን ማድረግ የሚየስችሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅ የሚከበር መሆኑ ለየት ያደርገዋል ነው ያሉት፡፡   20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በህብረብሔራዊ አንድነት የደመቀ ብዝሀነትን ለዓለም ገልጸን የምናሳይበት ነው ያሉት አፈጉባዔው ሁሉም ማንነቶች እኩል የሚስተናገዱበት እውነተኛ የፌዴራል ስርዓት በመገንባት ሂደት አዲስ ታሪክ እጥፋት ላይ መሆናችንን የምናሳይበት ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ከኩስመና ዘመን ወደ ማንሰራራት፤ ከቁዘማ ወደ መነቃቃት፤ ከጨለማ ወደ ተስፋ ብርሃን የተሸጋገርን መሆኑን የምናሳይበት ነውም ብለዋል በመልዕክታቸው፡፡ ቀኑ በመከባበር፤ በመደጋገፍ፤ በእኩልነትና በአንድነት በመኖር በጋራ የመልማት ቃል ኪዳናችንን የምናድስበት ቀን ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡ ይህንን የጋራ ኢትዮጵያዊ ማንነት ለማጽናትና የህዝቦች የዘመናት አብሮነት እንደተጠበቀ ለማዝለቅ በህብረ ብሔራዊነት ላይ የተመሰረተ አሰባሳቢ ትርክት መገንባት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል፡፡
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ የክልሉ ሕዝብ ቁርጠኛ ነው -እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)
Dec 8, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ የክልላችን ሕዝብ ትጋቱን ይቀጥላል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ። ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ሃሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ እየተከበረ የሚገኘው “ዴሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሐሳብ ነው። በዚሁ ወቅት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ በዓሉ ብሔራዊ መግባባትን በማጠናከር የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን ለማሳለጥ ከፍተኛ ፋይዳ አለው ብለዋል። በተጨማሪም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በአንድ መድረክ ተገኝተው እንዲደምቁና እንዲመክሩ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ነው ያሉት። ኢትዮጵያውያን ባህላዊ ትውፊታቸውንና ልምዶቻቸውን የሚለዋወጡበት ዕድል መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።   ለወንድማማችነትና እህትማማችነት ዕሴቶች ማበብ እንዲሁም ለኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ፌዴራሊዝም መዳበር ብሎም ለጋራ ትርክት ግንባታ በዓሉ የራሱን አስተዋጽኦ ማበርከቱን ቀጥሏል ብለዋል። ቀኑ በሐሳብ ልዕልና በመመራት ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት የመመካከርና የመወያየት ባህልን በማላቅ የዳበረ የዴሞክራሲና የአካታችነት ባህልና እሴቶችን ለማስረጽ እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ ይወሰዳል ሲሉም ገልጸዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን በጋራ ጥረት እውን በማድረግ ሀገራችን ክብሯ የተሟላ እንዲሆን የብልጽግና ጉዞዋም እንዲሳካ የተጀመሩ ጥረቶች እንደ ክልል ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የሀገራችንን ብሔራዎ ጥቅሞች ለማስከበርና አዳጊ የሕዝቦች ፍላጎትን ለማሟላት መሠረታዊ ሆኑ እንደ ባሕር በር ያሉ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ በሚደረገው እንቅስቃሴ የክልላችን ሕዝቦች የበኩላቸውን ለመወጣት ቁርጠኛ ናቸው ብለዋል በንግግራቸው። ቀኑ በክልላችን መከበሩ ለክልላችን ዘርፈ ብዙ ፋይዳና ትርጉም እንዳለውም እንገነዘባለን ነው ያሉት።
ፖለቲካ
20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በውጭ በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ተከበረ
Dec 8, 2025 96
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች ተከብሯል። በዓሉ የተከበረው "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ነው። በአከባበሩ ላይ የሚሲዮን መሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና ሰራተኞች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የማህበረሰብ ተወካዮችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ኢትዮጵያ የብዝኃነት ተምሳሌት እና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ባሳየ መልኩ ተከብሯል። የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦችና አልባሳት ለእይታ የቀረቡ ሲሆን የብሔሮች ብሔረሰቦች ሙዚቃዎችና ባሕላዊ ውዝዋዜዎች የሚገልጹ ሁነቶችም ቀርበዋል። በዓሉ በቻይና፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ቱርኪዬ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኳታር፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቤልጂየም፣ ፓኪስታን፣ ኮትዲቭዋር፣ ስዊድን፣ ኮሪያ ሪፐብሊክ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ አውስትራሊያ፣ ዩጋንዳ፣ ሩዋንዳ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ ቀኑ ከተከበረባቸው ሀገራት መካከል ይገኙበታል። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ዛሬ ተከብሯል።
ብልጽግና ፓርቲ ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ
Dec 8, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ብልጽግና ፓርቲ ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ፓርቲው ያስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡- እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አደረሰን አደረሳችሁ! የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በየደረጃውና በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር ቆይቶ በዛሬው ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በደማቅ የማጠቃለያ መርሀግብር እየተገባደደ ይገኛል፡፡ የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ከህዳር 01 ጀምሮ ለተከታታይ አንድ ወር በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በደማቅ ኩነት እንዲከበር ተደርጓል፡፡ ይህም እውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት እና ፌዴራላዊ ሥርዓት ለመገንባት የተያዘው ቁርጠኝነት ማሳያ ነው፡፡   ብልፅግና ፓርቲና የመደመር መንግሥት 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ከዕለታዊ ክብረበዓል በላይ የአጀንዳው ትክክለኛ አስፈላጊነት በውል በመረዳት በበዓሉ ስያሜ የተገለጹትን የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የፍትህ፣ የእኩልነት፣ የልማትና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች በተግባር በመመለስ መሆን አለበት ብሎ ያምናል፡፡ ለዚህም በዓሉ በአንድ ቀን ከማክበር አንድ ወር ሙሉ በመውሰድ በየክልሉና ከተማ አስተዳደሩ ያሉት ባህሎችና ነባራዊ እውነታዎች ታሳቢ በማድረግ በተከታታይ እንዲከበር መደረጉ የዚህ እምነት አንዱ ማሳያ ነው፡፡ በዓሉ “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል እንዲከበር የተመረጠበት ምክንያት እውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት እና ፌዴራላዊ ሥርዓት የሚገነባው ዴሞክራሲያዊ መግባባት በመፍጠር መሆኑ በግልጽ አመላክቷል፡፡ ዴሞክራሲያዊ መግባባት ወይም የመግባባት ዴሞክራሲ የሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት ከሆኑ ዕሳቤዎችና ተግባራት አንዱ ሲሆን የሀገራችን የዘመናት ችግር እና የሥርዓት ስብራት ሆኖ የቆየውን የዴሞክራሲ ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ እየተተገበረ ያለ ዕሳቤ ነው፡፡ ዋነኛው የኢትዮጵያ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ጥያቄ የዴሞክራሲ ጥያቄ ነበረ፡፡ ከለውጡ በፊት በነበሩት ዓመታት ይህንን በዓል የዕሳቤ ጥራት እና የተግባር ቁርጠኝነት ያልተፈጠረበት የይስሙላ የአደባባይ ትዕይንት ሆኖ ሲከበር ቆይቷል፡፡ ሙሉ ዕይታን መለያው ያደረገው ብልፅግና ፓርቲ ይህንን የዕይታና የተግባር ክፍተት በማረቅ የጎደሉትን የእውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት፣ ፌዴራላዊ ሥርዓት እና ዴሞክራሲያዊ መግባባት አላባውያን በማገናኘት ወደ ተቃና የለወጥና የዝላይ ምዕራፍ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ዴሞክራሲያዊ መግባባት የተዋንያን በተለይ ደግሞ የህዝብ ይሁንታና ተሳትፎ የሚያስተናግድ ዕሳቤና ማህበራዊ ውል ነው፡፡ የዴሞክራሲያዊ መግባባት አንዱና ዋነኛ መገለጫ ምርጫ ሲሆን የዘንድሮው የህዳር 29 በዓል ከ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ጋር ተያይዞ የሚታይ ነው፡፡ ያለፈው 6ኛ ሀገራዊ ምርጫ ለዴሞክራሲያዊ መግባባት መሠረት የጣለ ስኬታማ ምርጫ እንደነበረው ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ደግሞ የዚህ ዕሳቤና ማህበራዊ ውል የአፈጻጸም ከፍታ የሚታይበት እንዲሆን አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡ በዓሉ በያዝነው ዓመት ሲከበር የኢትዮጵያ ብልፅግና አይቀሬ ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ ፕሮጀክት መሆኑ በአያሌ ማሳያዎች የተረጋገጠበት በመሆኑ በዓሉ ይበልጥ ደማቅ አድርጎታል፡፡ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ መመረቅ ብልፅግና ፓርቲ ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር እንደሚፈጸም ማሳያ ነው፡፡ በዕለቱ የተበሰሩ 7ቱ በጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች ሆነው የዚህ ተግባር ቀጣይነት በማሳየት በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ መተማመንና ቅቡልነት ለመፍጠር ተችሎበታል፡፡ ይህ በመፍጠን፣ መፍጠርና ዝላይ የታጀበ አስደናቂ የልማት አርበኝነት የባህር በር አጀንዳችን ላይ ለመድገም ስንቅ በመሆን “ከግድቡ ወደ ባህሩ” በሚል ህዝባዊ መፈክር ከታሪካችንና ከማንነታችን አለአግባብ የተወሰደብንን የባህር በር ጥያቄያችን በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለማስመለስ እንደ ህዝብና ሀገር አንድ ሆነን እየሰራንበት እንገኛለን፡፡ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ስናከብር የመደመር መንግሥት ያስቀመጣቸውን አሻጋሪና ተስተካካይ ዕቅዶች እየተተገበሩና ውጤት እያመጡ መሆናቸውና ለዚህም ህዝብ በባለቤትነት የሚሳተፍበትና ተጠቃሚ እየሆነበት ያለ መሆኑ በመገንዘብ ነው፡፡ በቀጣይ ዓመት 21ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የምናከብረውም በአንድ እጃችን የጀመርናቸው የፀጥታና የልማት ሥራዎች አሳክተን በሌላው እጃችን ደግሞ ህዝቦች ለዘመናት የታገሉለትን የዴሞክራሲ ሥርአት ወደ ላቀ ደረጃ አድርሰን ነው፡፡ በጉጉት የሚጠበቀውና ነጻ፣ ፍትሀዊና አሳታፊ በመሆን የዴሞክራሲ እመርታ እንዲፈጠርበት በሚጠበቀው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች እንደ ከዚህ ቀደሙ በባለቤትነትና በላቀ ተነሳሽነት በመሳተፍ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሀገራችን ፀጥታ፣ ልማትና ዴሞክራሲ የሚጎመዝዛቸው ባዳዎችና ባንዳዎች ሀገር አፍራሽ እንቅስቃሴዎቻቸውን በንቃት በመከታተልና በመመከት እንዲሁም በዛሬው ቀን በድምቀት እያጠቃለልነው ያለነው በዓል መሪ ቃል የሆነውን “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” ተግባራዊ ለማድረግ ዴሞክራሲያዊ መግባባታችንን እና ህብረብሄራዊ አንድነታችንን በማጽናት መሆን አለበት፡፡ መልካም 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል! ብልፅግና ፓርቲ ህዳር 29፤ 2018 ዓ.ም
ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Dec 8, 2025 96
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል መንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፣ የክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች በበዓሉ ላይ ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአባቶቻችን ደም የወረስነውን ነጻነት በብልጽግና ማጽናት ከትውልዱ የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬ ላይ ከተሞች እያደጉ የገጠር መንደሮች ለመሻገር በትጋት እየሰሩ ያሉበት ወቅት መሆኑን ገልጸው፤ ታሪካዊ ቅርሶችም አቧራቸውን አራግፈው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ኩራት መሆናቸውን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ክረምት ከበጋ በማረስ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች መሆኑን ገልጸው፤ የወረስነውን ነጻነት ብቻ ሳይሆን የተሸከምነውን የትውልድ አደራ ማሰብ ይኖርብናል ብለዋል። ብልጽግናን ማሳካት ፈታኝ ሂደት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ማየት እንደሚገባ ተናግረዋል።   ትውልዱ ኢትዮጵያ ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ፈልፍሎ የማየት እና የማውጣት አቅም እንዳለው በጅምር ስራዎች መታየቱን አንስተዋል። በትብብር መንፈስ በብዙ ትጋት እና ልፋት አዲስ የታሪክ ገጽ መክፈት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ብልጽግና ምሉዕነት የሚረጋገጠው ኢትዮጵያውያን በህብረት መትጋት እና መስራት ሲችሉ መሆኑን አመልክተዋል። መተባበርን፣ መከባበርን እና በጋራ መቆምን እንዲሁም ብሔራዊ ጥቅምን የሁላችን ሀብት እና ስንቅ ማድረግ አለብን ብለዋል። የሀገርን መሻት እና የባዳን ክፋት መለየት እንደሚገባ ገልጸው፤ ኢትዮጵያውያን የባዳ ፍላጎት መሳሪያ መሆን እንደሌለባቸው ጠቁመዋል። የሀገርን ጥቅምና የህዝብ ክብር ማስቀደም እንደሚገባ ገልጸው፤ ለዘመናዊነት እና ለውጥ ክፍት መሆን እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ብዙ ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ አስደናቂ ውጤት በማስመዝገብ እያንሰራራች ትገኛለች ብለዋል። ይህን መልካም ጅማሮ ለማደናቀፍ ሙከራዎች መኖራቸውን ገልጸው፤ ማንኛውም ፈተና፣ ትንኮሳ እና ክፉ ሀሳብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ማቆም አይችልም ብለዋል።
መንግስት ሁለንተናዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ  ብዝኃነትን ከአንድነት ጋር የሚያስማማ መንገድ መርጦ በትኩረት እየሰራ ነው 
Dec 8, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት ሁለንተናዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ብዝኃነትን ከአንድነት ጋር የሚያስማማ መንገድ መርጦ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት "ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሐሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል፡፡   የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ብዝኃ ማንነት፣ ቋንቋ እና ባህል የሚገለጽበት ይህ በዓል በርካታ ዓላማዎችን አንግቦ እየተከበረ ይገኛል ብለዋል፡፡ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እርስ በእርሳቸው እንዲተዋወቁ፣ ባህላቸውንና ልምዶቻቸውን እንዲለዋወጡ ብሎም ህብረ-ብሔራዊ አንድነታቸውን ማጠናከር ማስቻሉን ገልጸዋል። የዘንድሮው በዓል ከቀደሙት የሚለየው "ዳግማዊ ዓድዋ" የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተመረቀበት እና የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች ጅማሮ በተበሰረበት ማግስት መከበሩ መሆኑንም አንስተዋል። በህብረ ብሔራዊ አንድነት የደመቀ ብዝኃነታችንን ለዓለም ገልጸን የምናሳይበት ቀን ነው ያሉት አፈ-ጉባኤው፤ እውነተኛ የፌዴራል ሥርዓት በመገንባት ሂደት አዲስ የታሪክ እጥፋት ላይ መሆናችንን የምናስገነዝብበት ነው ብለዋል፡፡   ለብዝኃነት ክብር የሚሰጥ የጋራ ማንነት እንዲኖር መስራት ይገባል ያሉት አቶ አገኘሁ፤ የጋራ ማንነትን ለማጽናትና በብሔራዊነት ላይ የተመሰረተ አሰባሳቢ ትርክት መገንባት እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ መንግስት ሁለንተናዊ ብልጽግናንን እውን ለማድረግ እና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ብዝኃነትን ከአንድነት ጋር የሚያስማማ መንገድ መርጦ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ይህንን እውን ከማድረግ አኳያም የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡
የበዓሉ መከበር የጋራ ትርክትን ለመገንባት እየተደረገ ያለውን የሀገራዊ ምክክር ሂደት ፍሬያማ ያደርገዋል- እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Dec 8, 2025 90
ሆሳዕና፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል መከበር የጋራ ትርክትን ለመገንባት እየተደረገ ያለውን የሀገራዊ ምክክር ሂደት ፍሬያማ እንደሚያደርገው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በሆሳዕና ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡   በበዓሉ ላይም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ የበዓሉ መከበር የጋራ ትርክትን ለመገንባት እየተደረገ ያለውን የሀገራዊ ምክክር ሂደት ፍሬያማ ያደርገዋል። በዓሉ የዳበረ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር የሀገረ መንግሥት ግንባታን በማጠናከር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል፡፡ በዓሉ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ባህላዊ ትውፊቶቻቸውን ከመለዋወጥ በተጨማሪ የእርስ በእርስ ትስስርን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል፡፡   በዓሉ የዘመናት ቁጭት ሆኖ የቆየውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በማጠናቀቅ ሌሎች አዳዲስ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ማግስት መከበሩ የተለየ ያደርገዋል ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የክልሉ ህዝብ ከሌሎች ህዝቦች ጋር በአብሮነት በመኖር የሚታወቅ ህዝብ መሆኑን ጠቅሰው ክልሉ ያለውን እምቅ አቅም በአግባቡ በመጠቀም ለሀገር ህልውና መጠበቅ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል፡፡ በተያያዘም 21ኛው የብሄሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ እንደሚዘጋጅ የተጠቆመ ሲሆን በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር እና በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ መካከል የሰንደቅ ዓላማ ርክክብ ተካሄዷል፡፡   በተመሳሳይም በበዓሉ አከባበር ስነ-ስርዓት ላይ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅን ተከትሎ የዋንጫ ርክክብ ስነ- ስርዓት ተካሄዷል፡፡ የዋንጫ ርክክቡን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) ለኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር አስረክበዋል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዓሉ የህዝቦችን ህብረብሔራዊ አንድነትና አብሮ የመኖር እሴት በማጠናከር በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል 
Dec 8, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፡- ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዓሉ የህዝቦችን ህብረብሔራዊ አንድነትና አብሮ የመኖር እሴት በማጠናከር ዘላቂ ልማትና ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ሃሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል።   በበዓሉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፤ ምክር ቤቱ የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን እንዲከበር ሲወስን ብሔር ብሔረሰቦች አርስ በእርሳቸው እንዲተዋወቁ፤ ባህላዊ እሴቶቻቸውንና መልካም ልምድና ተሞክሮዋቻቸውን እንዲለዋወጡና ህብረብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዘላቂ ሰላም ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለልማት በጋራ እንዲቆሙ ማድረግም እንዲሁ፡፡ ባለፉት 19 ዓመታት በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በተለያዩ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አስተናጋጅነት በዓሉ ሲከበር መቆየቱን ያስታወሱት አፈጉባዔው ይህም በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቦችን ህብረብሔራዊ አንድነትና አብሮ የመኖር እሴት በማጠናከር የሀገረ መንግስት ግንባታውን እና ዘላቂ ልማትና ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉንም አውስተዋል፡፡ የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የጋራ ትርክት ውጤት የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተጠነቀቀበት ወቀት የሚከበር መሆኑና የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞን እውን ማድረግ የሚየስችሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅ የሚከበር መሆኑ ለየት ያደርገዋል ነው ያሉት፡፡   20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በህብረብሔራዊ አንድነት የደመቀ ብዝሀነትን ለዓለም ገልጸን የምናሳይበት ነው ያሉት አፈጉባዔው ሁሉም ማንነቶች እኩል የሚስተናገዱበት እውነተኛ የፌዴራል ስርዓት በመገንባት ሂደት አዲስ ታሪክ እጥፋት ላይ መሆናችንን የምናሳይበት ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ከኩስመና ዘመን ወደ ማንሰራራት፤ ከቁዘማ ወደ መነቃቃት፤ ከጨለማ ወደ ተስፋ ብርሃን የተሸጋገርን መሆኑን የምናሳይበት ነውም ብለዋል በመልዕክታቸው፡፡ ቀኑ በመከባበር፤ በመደጋገፍ፤ በእኩልነትና በአንድነት በመኖር በጋራ የመልማት ቃል ኪዳናችንን የምናድስበት ቀን ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡ ይህንን የጋራ ኢትዮጵያዊ ማንነት ለማጽናትና የህዝቦች የዘመናት አብሮነት እንደተጠበቀ ለማዝለቅ በህብረ ብሔራዊነት ላይ የተመሰረተ አሰባሳቢ ትርክት መገንባት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል፡፡
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ የክልሉ ሕዝብ ቁርጠኛ ነው -እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)
Dec 8, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ የክልላችን ሕዝብ ትጋቱን ይቀጥላል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ። ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ሃሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ እየተከበረ የሚገኘው “ዴሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሐሳብ ነው። በዚሁ ወቅት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ በዓሉ ብሔራዊ መግባባትን በማጠናከር የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን ለማሳለጥ ከፍተኛ ፋይዳ አለው ብለዋል። በተጨማሪም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በአንድ መድረክ ተገኝተው እንዲደምቁና እንዲመክሩ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ነው ያሉት። ኢትዮጵያውያን ባህላዊ ትውፊታቸውንና ልምዶቻቸውን የሚለዋወጡበት ዕድል መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።   ለወንድማማችነትና እህትማማችነት ዕሴቶች ማበብ እንዲሁም ለኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ፌዴራሊዝም መዳበር ብሎም ለጋራ ትርክት ግንባታ በዓሉ የራሱን አስተዋጽኦ ማበርከቱን ቀጥሏል ብለዋል። ቀኑ በሐሳብ ልዕልና በመመራት ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት የመመካከርና የመወያየት ባህልን በማላቅ የዳበረ የዴሞክራሲና የአካታችነት ባህልና እሴቶችን ለማስረጽ እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ ይወሰዳል ሲሉም ገልጸዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን በጋራ ጥረት እውን በማድረግ ሀገራችን ክብሯ የተሟላ እንዲሆን የብልጽግና ጉዞዋም እንዲሳካ የተጀመሩ ጥረቶች እንደ ክልል ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የሀገራችንን ብሔራዎ ጥቅሞች ለማስከበርና አዳጊ የሕዝቦች ፍላጎትን ለማሟላት መሠረታዊ ሆኑ እንደ ባሕር በር ያሉ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ በሚደረገው እንቅስቃሴ የክልላችን ሕዝቦች የበኩላቸውን ለመወጣት ቁርጠኛ ናቸው ብለዋል በንግግራቸው። ቀኑ በክልላችን መከበሩ ለክልላችን ዘርፈ ብዙ ፋይዳና ትርጉም እንዳለውም እንገነዘባለን ነው ያሉት።
ማህበራዊ
ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ይካሄዳል-ኢንስቲትዩቱ
Dec 8, 2025 85
አዳማ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ )፡- ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የክትባት ዘመቻውን ለማሳካት ያለመ የባለድርሻ አካላት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።   በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች ቅኝትና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክተር አቶ እንዳለ ዘመነ እንደገለጹት፤ ፖሊዮን ለማጥፋት የተቀናጀ ሀገር አቀፍ ክትባት ዘመቻ በመላው ሀገሪቱ ይካሄዳል። ዘመቻውን ስኬታማ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የክትባት ዘመቻው 25 ሚሊዮን የሚሆኑ ሕፃናት ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በሁሉም ክልሎች የክትባቱ ቁሳቁስና ተያያዥ ግብዓት አቅርቦት በየወረዳዎቹ የጤና ተቋማት ደርሰው ወደ ቀበሌዎች እየተሰራጩ እንደሚገኙ አንስተው፤ የሰው ሃይል ዝግጅትን ጨምሮ የሕብረተሰብ ንቅናቄ መካሄዱንም አክለዋል።   በዘመቻው የቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት ከመስጠት ጎን ለጎን የበሽታው ምልክት ያሳዩትን ሕፃናት የመለየት ስራ እንደሚከናወን አስረድተዋል። በጤና ሚኒስቴር የክትባት ፕሮግራም የኮሙኒኬሽን አማካሪ ወይዘሮ ፀጋነሽ ገድሉ እንዳመለከቱት፤ በዘመቻው መደበኛ የፖሊዮ ክትባት ያልወሰዱ ሕፃናት ይካተቱበታል። በጊዜያዊ የክትባት ጣቢያዎችና ወደ ጤና ተቋማት ሄደው ክትባቱን እንዲወስዱ የማድረግ ስራ ይሰራል ነው ያሉት ።   ክትባቱ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ከተሞች፤ ወረዳዎችና ቀበሌዎች በተመሳሳይ ወቅት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ ለስኬታማነቱም በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ትብብርና ዕገዛ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል ።  
የመደመር መንግሥት እይታ በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር ፈጥሯል
Dec 8, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት እይታ በኦሮሚያ ክልል ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር መፍጠሩን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። የዓለም ቱሪዝም ቀን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ለ21ኛጊዜ “ቱሪዝምና ዘላቂ ለውጥ” በሚል መሪ ሃሳብ በክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አዘጋጅነት በምሥራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ከተማ ተከብሯል።   የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን ታምሩ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሀብቶች ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ተደርጓል። የመደመር መንግሥት እይታ በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሃብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር መፍጠሩን ገልጸው፤በክልሉ ያሉ ሁሉም ወረዳዎች የራሳቸው የቱሪዝም መዳረሻ እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት። የምስራቅ ባሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጃርሶ ቦሩና በበኩላቸው ዞኑ በርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ሃብቶች እንዳሉት ተናግረዋል።   ለአብነትም የሶፍ ዑመር ዋሻ፣ ድሬ ሼህ ሁሴን፣ አስደናቂ መልክዓ ምድሮች እና ጥቅጥቅ አረንጓዴ አካባቢዎች እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። ከዚህ ቀደም በአካባቢው የሚገኙትን ሃብቶች በማልማት ረገድ ምንም እንዳልተሰራ አንስተው፤ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በፌዴራልና በክልሉ መንግሥት ሰፋፊ መሠረተ ልማቶች በትኩረት እየተገነቡ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ የመንገድ፣ የመብራት፣ የቴሌኮም ኔትወርክን ጨምሮ ቱሪዝምን የሚያነቃቁ መሠረተ ልማቶች በመገንባታቸው ዞኑ ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆን መቻሉን ተናግረዋል። መሠረተ ልማቶቹ በዞኑ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ ማገዛቸውን አስታውቀዋል።  
አዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ በስራ ገበያው ተፈላጊና ብቃት ያለው  የሰው ኃይል ለማፍራት ያስችላል
Dec 8, 2025 45
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018 (ኢዜአ):-አዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ በስራ ገበያው ተፈላጊና ብቃት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት እንደሚያስችል የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዲሱን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ በተመለከተ ለክልሎች፣ ለከተማ አስተዳደሮችና ለዘርፉ አስፈጻሚ አካላት በቢሾፍቱ ከተማ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) በስልጠና ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ እንዳሉት፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በእውቀትና በክህሎት የበቃ የሰው ኃይል ማፍራት ያስፈልጋል።   ለዚህም ጠንካራ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን መገንባት እንደሚያስፈልግ ገልጸው፥ ሚኒስቴሩ አዲስ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። ስትራቴጂው ከዚህ ቀደም ከነበረው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጅ ትግበራ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን መነሻ በማድረግ ከሀገር አቀፍ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ጋር እንዲጣጣም ተደርጎ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። ስትራቴጂው በፍጥነት እየተለዋወጠ ካለው የስራ ገበያ ፍላጎት ጋር ብቁ ሆኖ ለመገኘት እና የወጣቱን እምቅ የፈጠራና የክህሎት አቅም አሟጦ ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት በፋይናንስ ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያስችል በሂደትም ወደ ራስ ገዝነት የሚያሸጋግር መሆኑን አንስተዋል።   የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አስተዳደርን በማጎልበት የስልጠና አግባብነትንና ጥራትን እንደሚያሻሽልና ለስራ ዝግጁ የሚያደርጉ ክህሎቶችን ለማዳበር እንደሚያግዝም እንዲሁ። ስልጠናው በሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የዘርፉ ተቋማት በስትራቴጂው ላይ የጋራ ግንዛቤ ይዘው ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ በማለም የተዘጋጀ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ለ4ኛው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ  ውጤታማነት የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፉ ሚናውን ማጠናከር ይጠበቅበታል
Dec 8, 2025 50
ባሕርዳር፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል 4ኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ውጤታማ እንዲሆን የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፉ ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ሚናውን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅበት ተመላከተ። ‎‎በክልሉ የሚካሄደውን 4ኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻን አስመልክቶ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በባሕርዳር ከተማ ተካሂዷል።   ‎‎በመድረኩ ላይ የክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ስሜነህ አያሌው እንዳስታወቁት፤ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻው ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም በክልሉ በሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ይካሄዳል። ‎ክትባቱ የሚሰጠው ‎የፖሊዮ በሽታ ምልክት በመታየቱ እንደሆነ አንስተው፤ በሽታው ህፃናትን ለሞትና ለአካል ጉዳት የሚዳርግ ተላላፊ በመሆኑ በመከላከል ለማጥፋት ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ከመደበኛው ክትባት በተጨማሪ ዕድሜያቸው ከ10 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ከዚህ ቀደም ቢከተቡም ባይከተቡም ክትባቱን እንዲወስዱ ይደረጋል ብለዋል። ‎ይህም ቤት ለቤት፣ በመጠለያ ጣቢያዎች፣ በትምህርት ቤት፣ በጤና ተቋማትና በጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች ተፈጻሚ እንደሚሆን አስረድተዋል።   ‎‎በዘመቻውም የክትባት ቡድኖችና አስተባባሪዎች እንደሚሳተፉ ጠቁመው፤ ለ‎ዘመቻው ውጤታማነት የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፉን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠርና ድጋፍ በማድረግ ሚናቸውን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል። ወላጆችም ከ10 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ልጆቻቸውን በወቅቱ እንዲያስከትቡ ጥሪ አቅርበዋል። ‎‎የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አበበ ተምትም በበኩላቸው እንዳሉት፤ በክልሉ ተላላፊ በሽታዎችን አስቀድሞ በመከላከል ህፃናትን ከጉዳት ለመታደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።   ‎‎በክልሉ 15 ዓይነት የክትባት አገልግሎቶችን በተሟላ መንገድ በመስጠት የህፃናትን ጤና ለመጠበቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። ‎‎የፖሊዮ በሽታን ለማጥፋት እየተደረገ ያለው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን የሴክተር መስሪያ ቤቶች፣ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን እንዲሁም አጋር አካላት በቅንጅት በመስራት የድርሻቸውን እንዲወጡም መልዕክት አስተላልፈዋል። ‎‎በንቅናቄው መድረክ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የወጣቶችና ሴት አደረጃጀቶች ተሳትፈዋል።
ኢኮኖሚ
የስንዴ ልማቱ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ለተያዘው  ትልም መሳካት ትልቅ  ማሳያ ነው - የአመራር አባላት
Dec 8, 2025 30
ወላይታ፤ ሕዳር 29/2018 (ኢዜአ)፦ እየተከናወነ የሚገኘው የስንዴ ልማት የምግብ ዋስትናን በአጠረ ጊዜ ማረጋገጥ እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ መሆኑን በወላይታ ዞን ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ መካከለኛና ከፍተኛ አመራር አባላት ተናገሩ። "በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ በዞኑ ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ መካከለኛና ከፍተኛ አመራር አባላት በቦዲቲ ከተማ እና በዳሞት ጋሌ ወረዳ የስንዴ ልማት፣ የኢንዱስትሪ፣ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የአመራር አባላቱ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት፤ እየተከናወኑ የሚገኙ የስንዴ ልማት ስራዎች የምግብ ዋስትናን በአጠረ ጊዜ ማረጋገጥ እንደሚቻል ማሳያ ነው። አስተያየታቸውን ከሰጡ የአመራር አባላት መካከል ወይዘሮ መሰረት ሆጃሞ ስልጠናው ከመናገር በላይ ሰርተን ለመለወጥ የሚያስችል መስፈንጠሪያ አቅምን አግኝተንበታል ብለዋል። በሁሉም ዘርፎች እየመጡ ያሉ ውጤቶች የሚያስደስቱ መሆናቸውንና በስንዴ ልማቱ የተመዘገበው ስኬት በምግብ ሰብል ራስን ለመቻልና ከተመጽዋችነት ለመውጣት የተያዘው ውጥን እንደሚሳካ ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም በስልጠናውም ሆነ በጉብኝቱ ያገኙትን አቅም በማቀናጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት ለመስራት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ስልጠናው አመራሩ ሀገሩን አውቆ አቅሙን እንዲያወጣ ያግዛል ያሉት ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ አንዱዓለም ጌታሁን በወረዳው ያዩት ልማት ለሀገር ትልቅ ተስፋ ነው ብለዋል። በወረዳው አርሶ አደሩ በክላስተር በመደራጀት እያለማ የሚገኘው የስንዴ ልማት ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ የወላይታ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አማረ አቦታ (ዶ/ር) በዞኑ በግብርናው፣ በኢንዱስትሪው፣ በከተማ ልማትና በቱሪዝም እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ስልጠናውም በአመራሩ ዘንድ ቁጭት በመፍጠር የህዝቡን መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ተግቶ እንዲሰራ አቅም የሚፈጥር እንደሆነም ገልፀዋል። ያሉ ፀጋዎችን አሟጦ በመጠቀም የግብርናን ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ከዚህ ቀደም ምርት የማይሰጡ ማሳዎችን በኖራ በማከም፣ በመስመር በመዝራትና ግብዓት በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን የመጨመር ስራ መሰራቱንም አስረድተዋል። ሰልጣኝ አመራር አባላቱ ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ተግዳሮቶችን ወደ ዕድል በመቀየር በየአካባቢው ያሉ እምቅ ፀጋዎችን በማልማት በሁሉም ዘርፎች እመርታ ለማስመዝገብ መትጋት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።  
የብረታ ብረት ኢንዱስትሪው እያመጣ ያለው ለውጥ የገጠርና የከተማ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ የሚያግዝ ነው
Dec 8, 2025 53
ባሕርዳር፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የብረታ ብረት ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያመጣ ያለው ለውጥ የተጀመረውን የገጠርና የከተማ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ የሚያግዝ መሆኑ ተገለጸ። በክልሉ ያሉ የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት አመራሮችና ባለሙያዏች የመንግስት የልማት ድርጅት የሆነውን የአማራ ብረታ ብረት ኢንዱስትሪና ማሽን ቴክኖሎጅ ኢንተርፕራይዝን ዛሬ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ዓላማውም የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት አመራሩና ባለሙያው በዘርፉ የገበያ ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ ያለውን ተግባር በማገዝ ሚናቸውን እንዲወጡ ለማነሳሳት እንደሆነ ተነግሯል።   በዚህ ወቅት የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ አባይ መንግስቴ እንዳሉት፤ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን አቅም በማሳደግ እድገቱን ለማፋጠን እየተሰራ ይገኛል። በተለይም የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት ለማሳደግና ከተሞችን ለማዘመን ቴክኖሎጂ ላይ መስራት መጠየቁን አስረድተዋል። ይህንን ለማሳካት የብረታ ብረት ኢንዱስትሪው ዘርፍ እየመጣ ያለውን ለውጥ የገጠርና የከተማ ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ገልጸዋል። በዚህም የአማራ ብረታ ብረትና ማሽን ቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ የኢንዱስትሪ መለዋወጫዎችን፣ አነስተኛ ማሽኖችን፣ ስማርት ፖሎችንና ሌሎች ግብአት እያመረተ መሆኑን አስረድተዋል። የኢንተርፕራይዙ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘላለም በላይ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢንተርፕራይዙ የአምራች ኢንዱስትሪውን ችግር ለማቃለል እየሰራ ይገኛል። ለአብነትም የፋብሪካዎችን መለዋዎጫዎች በማምረት የኢንዱስትሪውን ዘርፉ እያሳደገ መሆኑን አንስተዋል። ከውጭ የሚገቡ የኢንዱስትሪና ፋብሪካዎች ግብአት አምርቶ በማቅረብ የክልሉን ብሎም የሀገሪቱን እድገት ለማፋጠን ኢንተርፕራይዙ የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።   ኢንተርፕራይዙ ከሚያመርታቸው ውስጥ ትራንስፎርመር፣ ማረሻ፣ ተንጠልጣይ ድልድይ እና ስማርት ፖል እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። ቴክኖሎጅን የማላመድ፣ የመፍጠርና የማበዛት ስራ በማከናወን የውጭ ምንዛሬን ለማዳን ትኩረት መስጠቱን አመልክተዋል። በቀጣይ የውሃ ፓንፕ፣ የመኖ ማቀነባበሪያ፣ አነስተኛ ትራክተር፣ የበቆሎ መፈልፈያና ሌሎች ማሽነሪዎችን ለማምረት አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱንም ጠቁመዋል። ኢንተርፕራይዙ ለ600 ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉንም አንስተዋል።
የልማት ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንሰራለን
Dec 8, 2025 52
ቦንጋ ፤ ሕዳር 29/2018 (ኢዜአ)፡-የልማት ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁጭት እንደሚሰሩ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አመራሮች ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ማጠቃለያ ላይ አመራሩ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት በመፍጠን፣ በመፍጠር፣ በማባዛትና በማጥራት መስራት እንዳለበት መመሪያ መስጠታቸው ይታወሳል። በስልጠናው ኢዜአ ያነጋገራቸው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አመራሮችም ስልጠናው በየአካባቢው ያሉ የልማት ፀጋዎችን ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅም እንደሆናቸው ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የካፋ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ሀብታሙ ገብረስላሴ እንደገለጹት በክልሉ ያሉ የተፈጥሮ ሀብቶችን አልምቶ ለኢንቨስትመንት ለማዋል ከምንጊዜውም በላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ገልጸዋል። በቀጣይ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ፈጠራና ፍጥነት በማከል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በስልጠናው ያገኙትን አቅም ወደተግባር እንደሚቀይሩ አረጋግጠዋል። በዞኑ ኢንቨስትመንትን በመሳብ የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ለማሳደግና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁጭት ይሰራል ሲሉም ገልጸዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ የዞኑ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ አዱኛ አዴሎ፣ በእጃችን ያለውን ሀብት ማየትና ማልማት ባለመቻላችን ብዙ ነገር እንዳጣን ስልጠናው አሳይቶናል ብለዋል። ከዚህ ችግር በመውጣት ከአካባቢው ሀብት የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ ማልማት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብና ለውጥ የታየባቸውንም ለማስቀጠል የሚችል የሰው ሀይል መፍጠር ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል። ስልጠናው በፈጠራና በፍጥነት እንዴት ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚቻል አቅም የገነቡበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ የካፋ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ንጉሴ ባዩ ናቸው። በተጨማሪም በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ እንዴት ማልማት እንደሚቻልና ውጤታማነትን በማስቀጠል የህዝብንተጠቃሚነት ለማሳደግ ዕውቀት ማግኘታቸውንም ተናግረዋል። ይህን መነሻ በማድረግም በቀጣይም በግብርና፣ በከተማ ልማት፣ በቱሪዝምና በሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት እምርታዊ ለውጥ ለማምጣት በቁጭት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
ቡሳ ጎኖፋ ኦሮሚያ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ሊገነባ ነው
Dec 8, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ ቡሳ ጎኖፋ ኦሮሚያ አቅሙን የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችለውን የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ሊገነባ መሆኑን ገለጸ። በኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢዎች ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማት ምርታማነትን ማሳደግና ከተረጂነት የመውጣት እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል። ክልሎችም የአደጋ ጊዜ ዝግጁነታቸውን በማረጋገጥ ለችግር በራስ አቅም ምላሽ መስጠት የሚያስችል የተቀናጀ አቅም በመገንባት ላይ ይገኛሉ። የኦሮሚያ ክልልም ቡሳ ጎኖፋ የተሰኘ ተቋም አቋቁሞ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ችግሮችን ለመቋቋም እና አስቸኳይ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እየገነባ ይገኛል። የክልሉ ቡሳ ጎኖፋ ምክትል ኃላፊ አቶ ተፈሪ በየነ፣ ተቋሙ ከአባላት መዋጮ ከሚያገኘው ገቢ እና የግብርና ስራዎችን በማከናወን አቅሙን ለማጠናከር በክልሉ የተለያዩ ዞኖች ላይ ሰብል የማልማት ስራ እያካሄደ ነው። ይኸንኑ የግብርና ምርት በማቀነባበር ለሚፈለገው ዓላማ ለማዋል እንዲቻልም የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ሊገነባ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሁ መሰረት ጉዳዩን የሚያስተባብር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ተቋቁሞ የአዋጭነት ጥናት እና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል። በዚሁ መሰረት በቡልቡላ እና በነቀምቴ ግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገነቡት ሁለት ፋብሪካዎች የተቋሙን ስራ የሚያሳልጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በቡልቡላ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚገነባው ፋብሪካ በቀን ሁለት ሺህ ቶን ስንዴ የመፍጨት አቅም ያለው እና መኮሮኒና ፓስታንም የሚያቀነባብር መሆኑን አስረድተዋል። በነቀምቴ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ደግሞ በምግብ እጦት ለተጎዱ ለአስቸኳይ ጊዜ የሚውል አጋዠ ምግብ የሚቀነባበር መሆኑን ተናግረዋል። ፋብሪካዎቹ ቡሳ ጎኖፋ በራሱ አቅም የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፎችን ማድረግ እንዲችል የበለጠ አቅም የሚፈጥርለት መሆኑንም አውስተዋል። ቡሳ ጎኖፋ ምርት ማምረት ብቻ ሳይሆን በቂ ማከመቻ መጋዘኖች ሊኖሩት እንደሚገባ ታምኖ በአዳማ እና ሻሸመኔ ከተሞች የራሱ መጋዘኖች ማዘጋጀቱንም አውስተዋል። በቀጣይም በምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ከተማ እንዲሁም በምስራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ የመጋዘን ግንባታዎች ይከናወናሉ ብለዋል። ከዚህ ጎን ለጎን በሁሉም ዞኖች እና ወረዳዎች መጋዘን እንዲዘጋጅ አቅጣጫ መቀመጡንና ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ልማት ለሰላማዊ አገልግሎት ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል ነው 
Dec 8, 2025 106
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ልማት መርሃ ግብር ለሰላማዊ አገልግሎት ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል መሆኑን የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ ገለጹ። የኢትዮጵያን የኒውክሌር ኃይል ልማት መርሃ ግብር ማስጀመሪያና የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን ሥራ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረክ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ፣ የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሚካኤል ቹዳኮቭና የባለድርሻ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ ፤ የኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ልማት የኃይል ደህንነትን በማረጋገጥ የኢኮኖሚያዊ ሽግግርና የረጅም ጊዜ የመቋቋም አቅም ግንባታ ላይ የተመሠረተ ብሔራዊ የልማት ተነሳሽነት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ንጹህ የኃይል አቅርቦት የማመንጨት አቅምን በማላቅ በጤና፣ ግብርና፤ በኢንዱስትሪ እና የምርምር ትግበራ ማዕቀፍ የተቃኘ መሆኑን ገልጸዋል። የሰላማዊ አማራጭ የኒውክሌር ሳይንስ ልማት መርሃ ግብሩ ዓላማ የኢትዮጵያዊያንን ህይወት በተጨባጭ የሚያሻሽሉ ጥቅሞችን የሚያስገኝ ዕድል ማረጋገጥ እንደሆነም ተናግረዋል።   የኃይል አቅርቦት የዕድገት ሞተር ነው ያሉት ኮሚሽነሩ የሰላማዊ አማራጭ አስተማማኝ የኒውክሌር ኃይል ልማት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን ዕድገት ጥራትና ፍጥነት ይቀርፃል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የኒውክሌር ኃይል ልማት ቁርጠኝነት ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ ታሳቢ ያደረገ ደፋር ውሳኔ መሆኑን አብራርተዋል። በ​ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ በጉባ ከተበሰሩ ማግስት በሩሲያ የተካሄደው ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል መድረክ ድረስ ኢትዮጵያ ለሰላማዊ የኒውክሌር ልማት ያላትን ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን አስታውሰዋል። በዚህም ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ አገልግሎት ብቻ ለመጠቀም ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነች ብለዋል። ​የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን በተሰጠው ግልጽ ሥልጣንና ጠንካራ መዋቅር ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። ​የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር የተፈጠረው የሥልጠና ፕሮግራምና የባለሙያ የልምድ ልውውጥ፣ ክህሎት ግንባታና የቴክኒክ ትብብር እየተሳለጠ መሆኑን ተናግረዋል። ​በቀጣይም ኢትዮጵያ በዕውቀትና በሰላማዊ የኒውክሌር ልማት የጋራ ርዕይ በመመስረት ከዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር የትብብር ስራን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ልማት መርኃ ግብር ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ማዕቀፎች ጋር በማጣጣም የሚተገበር ነው 
Dec 8, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ልማት መርኃ ግብር ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ማዕቀፎች ጋር በማጣጣም የሚተገበር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያን የኒውክሌር ኃይል ልማት መርኃ ግብር ማስጀመሪያና የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን ሥራ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የሰው ልጆች ስልጣኔ ከእሳት፣ ውኃ፣ ነፋስና እንፋሎት የኃይል አማራጭ ልማት ጋር የተቆራኘ ነው። የኃይል አቅርቦት የቴክኖሎጂ ግኝቶች ከኢኮኖሚ ልማት ጋር የተቆራኘ አስተማማኝና ተመጣጣኝ የማኅበረሰብ ዕድገት ለመፍጠር አቅም እንዳላቸው ገልጸዋል። ​ ኢትዮጵያም በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ቴክኖሎጂ ልማት በአዲስና አስፈላጊ የኢንዱስትሪ አብዮት ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ተናግረዋል። ​የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ልማት በአስተማማኝ፣ የረጅም ጊዜና ንጹህ የኃይል ምንጭነት ከፍተኛ ትኩረት እያገኘ መምጣቱን አንስተዋል። የኒውክሌር ኃይል ለዘላቂ ብልጽግና መሠረት ነው ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገትና ብዙ የሕዝብ ቁጥር የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የረጅም ጊዜና ስትራቴጂካዊ የመሠረ ልማት ግንባታ ኢንቨስትመንቶችን ማስፋት አስፈላጊ ሆኗል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል ልማት መርኃ ግብር በጤና፣ በግብርና እና በሌሎች የልማት መስኮች ትግበራ የኃይል ፍላጎትን በማሟላት ብልጽግናን የማረጋገጥ ትልም ያነገበ መሆኑን አስገንዝበዋል። ​ የሰላማዊ ኒውክሌር ልማት መርሃ ግብርም የምንፈልጋትን ኢትዮጵያ እውን የሚያደርግ ብሔራዊ የልማት ፕሮጀክት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ ዳታ ማዕከላት፣ ባቡሮችና ተሸከርካሪዎች እንደ ኒውክሌር ኃይል ባሉ ከታዳሽና አስተማማኝ የኃይል ምንጮች በሚገኝ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩባት ሀገር የማድረግ ጉዞም በወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋርም የኢትዮጵያን ብሔራዊ የኒውክሌር ልማት መርሃ ግብር የደህንነትና ግልጽነት ደረጃ ለማስጠበቅ እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ልማት ውጥኗን ከጀመረች ማግስት አንስቶም የዓለም አቀፍ በአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ እየሰጠ ለሚገኘው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሌር ልማት መርሃ ግብር ጠንካራ ትብብር ላይ በመመስረት ከዓለም አቀፍ መስፈርቶች፣ ደረጃዎችና የዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ማዕቀፎች ጋር ሙሉ በሙሉ በማጣጣም የሚተገበር መሆኑንም ተናግረዋል። የአፍሪካ ኩራት የኢትዮጵያ የአቬሽን ኢንዱስትሪ እና የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬትም በሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል አማራጭ ያላትን የብልጽግና ተምሳሌት ሕልም ለማሳካት እንደሚሰራ ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽነር ሳንዶካን ደበበ፣ የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሚካኤል ቹዳኮቭና የባለድርሻ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በኦሮሚያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማስፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው
Dec 7, 2025 115
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል በ5 ከተሞች የተጀመረውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማስፋት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ዳመጠው ገመቹ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የክልሉ መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን በሙሉ አቅም ተግባራዊ ለማድረግ አቅጣጫ አስቀምጧል። በዚህ መሰረት ክልሉ ለሪፎርሙ ተግባራዊነት ያለውን ምቹ ሁኔታዎችን በመጠቀም የሚያስፈልጉ ሰነዶችን በማሟላት የዝግጅት ምዕራፍ አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸዋል። በተለይም ሪፎርሙ በክልሉ በፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ፣ በጤና ቢሮ፣ በትምህርት ቢሮ፣ በገንዘብ ቢሮና በአጠቃላይ በ5 የመንግስት መስሪያ ቤቶች በቀጣይ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑንም አንስተዋል። ከነዚህም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንዱ ሲሆን የክልሉን ህዝብ ከእንግልትና ካልተገባ ወጪ በማዳን ፈጣን፤ ቀልጣፋና ግልጽነት ያለው የተሻለ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።   ሪፎርሙን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ደግሞ የሰው ሀይል ማሰልጠን ፣ መሰረተ ልማቶችን ማሟላት፣ ቴክኖሎጂዎቹን ማበልጸግና ግንባታዎችን ማስፋትና ለተገልጋዩ የግንዛቤ ፈጠራ መስጠት ከሚተገበሩት ዋና ዋና ተግባራት መካከል መሆናቸውን አቶ ዳምጠው ገልጸዋል። በዚህ መሰረት በ2018 በጀት አመት በአንደኛ ዙር በሸገር፤ በቢሾፍቱ፤ በአዳማ፤ በሻሸመኔና ጅማ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩን አስታውቀዋል። አገልግሎቱ ከተጀመረ ወዲህ ባለፉት 3 ወራት 180 ሺህ ዜጎች አገልግሎቱን በማግኘት የእርካታ መጠናቸው ከ95 በመቶ በላይ መሆኑን በተደረገ የዳሰሳ ጥናት መለየቱን አንስተዋል።   በክልሉ በበጀት አመቱ አገልግሎቱን አጠናክሮ በማስቀጠል በቀጣይ ከሸገር ከተማ ባሻገር በ13 ትልልቅ ከተሞች ስራው ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚሰጥ አብራርተዋል። በዚህም በሻኪሶ፣ ሞያሌ፣ ሸኖ፣ ነጆና ዶዶላ ከተሞች እንዲሁም በሁለቱ የአርሲ ዞኖች፤ በጅማ፣ በምስራቅ ሀረርጌና ምስራቅ ሸዋ ዞኖች አገልግሎቱ ተደራሽ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። በዘንደሮ አመት በኦሮሚያ ክልል በአጠቃላይ በከንቲባ ደረጃ በሚተዳደሩት በ52 ከተሞች በተሟላ መልኩ አገልግሎቱን ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተው በቀጣይ እስከ ቀበሌዎች ድረስ ስራው የሚቀጥል መሆኑንም ተናግረዋል።
የሀገርን ብልጽግና የሚያሳልጥ ችግር ፈቺ የፈጠራ አቅም እየጎለበተ ነው
Dec 6, 2025 134
አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ የሚያሳልጥ ችግር ፈቺ የፈጠራ አቅም እየጎለበተ መምጣቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩትና በኤስ.ኤን.ቪ ዓለም አቀፍ ድርጅት ትብብር ለ10 ቀናት የተካሄደው 6ኛው ሀገር አቀፍ ''ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር'' ተጠናቋል።   በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ፤ በውድድሩ ከተሳተፉ 251 የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ተወዳዳሪዎች ውስጥ አንድ መቶ የሚሆኑት ለሽልማት በቅተዋል ብለዋል። ''ማሰልጠን፣ መሸለምና ማብቃት” የሚል መሪ ሃሳብ በተሰጠው ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር የግብርና፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎች ምርታማነትን የሚያሻሽሉ የፈጠራ ስራዎች መቅረባቸውን ገልጸዋል። አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎችንም በመረጃ ቋት በማደራጀት በኢንተርፕርነርሽፕ ስታርት አፕ ፈጠራ የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት እያሳደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ የሚያሳልጥ ችግር ፈቺ የፈጠራ አቅም እየጎለበተ ነው ያሉት አቶ ሰለሞን፤ በፈጠራና ፍጥነት በዕውቀትና ክህሎት የበለጸጉ ዜጎችን የማፍራት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን (ዶ/ር)፤ ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር የኢትዮጵያዊንን ዕምቅ የፈጠራ ክህሎት በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያዊያን የፈጠራ ክህሎት ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና አጋዥ የሚሆንበትን የማበረታቻ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የፈጠራ ባለሙያዎችም የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች በትጋት በማለፍ ለበለጠ ውጤት እንዲበቁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቦሩ ካና በበኩላቸው፤ ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር ውጤታማ ስታርት አፖችን ማፍራት እያስቻለ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በኤስ.ኤን.ቪ ዓለም አቀፍ ድርጅት የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጁሊ ግርሃም፤ በውድድሩ የተመረጡ የፈጠራ ስራዎች ወደ ስራ እንዲገቡ በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። የፈጠራ ስራዎች ለኢትዮጵያ እድገት ማዕከል ሆነው እንዲቀጥሉ በትብብር እንሰራለን ብለዋል። በፈጠራ ውድድሩ በግብርና ፣ በጤና ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎችን የሚደግፉ የፈጠራ ስራዎች ተሸላሚ ሆነዋል። ከእነዚህም መካከል አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የፈጠራ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራቸው ለተኪ ምርት፣ ለግብርና ምርት ጥራት እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች ባማከለ መልኩ የሚኖረውን ጠቀሜታ ገልጸዋል። በቀጣይም የፈጠራ ስራቸውን በስፋት ወደ ገበያ ለማስገባትና የስራ ዕድልን ለማስፋፋት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።  
ስፖርት
በፕሪሚየር ሊጉ ዎልቭስ ከማንችስተር ዩናይትድ ይጫወታሉ 
Dec 8, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018 (ኢዜአ):- በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 15ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሃ ግብር በዎልቭስ እና ማንችስተር ዩናይትድ መካከል ዛሬ ይካሄዳል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ምሽት 5 ሰዓት ላይ በሞለኒው ስታዲየም ይደረጋል። ዎልቭስ በሁለት ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ማንችስተር ዩናይትድ በ22 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ክለቦች በፕሪሚየር ሊጉ ሲገናኙ የአሁኑ ለ21ኛ ጊዜ ነው።   ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 20 ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ 10 ጊዜ ሲያሸንፍ ዎልቭስ 7 ጊዜ ድል ቀንቶታል። 3 ጊዜ አቻ ወጥቷል። በ20ዎቹ ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ 24 ግቦችን ሲያስቆጥር ዎልቭስ 22 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች በነበራቸው ግንኙነት ማንችስተር ዩናይትድ ሶስት ጊዜ፣ ዎልቭስ ደግሞ ሁለት ጊዜ ጨዋታዎችን አሸንፏል። መጥፎ የውድድር ዓመት እያሳለፈ የሚገኘው ዎልቭስ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ተጋጣሚው ማንችስተር ዩናይትድ በጥሩ አቋሙ ለመቀጠል ሶስት ነጥብ ያስፈልገዋል። የ40 ዓመቱ ማይክል ሳልስበሪ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሶስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ  
Dec 8, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ የሁለተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ይደረጋሉ። ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከአዲስ አበባ ከተማ ይጫወታሉ። አዳማ ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው 10 ጨዋታዎች አራቱን ሲያሸንፍ አምስት ጊዜ ተሸንፏል። አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ ላይ ዘጠኝ ግቦችን ሲያስቆጥር 19 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ13 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው አዲስ አበባ ከተማ በሊጉ ማሸነፍ የቻለው ጨዋታ አንድ ብቻ ነው። ስምንት ጊዜ ሲሸንፍ አንድ ጊዜ አቻ ተለያይቷል። አምስት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 22 ግቦች ተቆጥረውበታል። በአራት ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሃ ግብር መቻል ከባህር ዳር ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በሊጉ ካከናወናቸው 10 ጨዋታዎች መካከል ስድስቱን ያሸነፈው መቻል ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 17 ግቦችን በ10ሩ ጨዋታዎች ላይ ሲያስቆጥር ሰባት ግቦችን አስተናግዷል። መቻል በ20 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ባህር ዳር ከተማ በውድድር ዓመቱ 10 ጨዋታዎችን አድርጎ አንድ ጊዜ አሸንፎ በስምንቱ ተሸንፎ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። አምስት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 15 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ባህር ዳር ከተማ በአራት ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። የዕለቱ የመጨረሻ መርሃ ግብር ልደታ ክፍለ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ያገናኛል። ልደታ ክፍለ ከተማ በሊጉ ባካሄዳቸው 10 ጨዋታዎች ያሸነፈው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በሰባቱ ሲሸነፍ ሁለት ጊዜ አቻ ወጥቷል። በ10ሩ ጨዋታዎች ላይ ሰባት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 19 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በአምስት ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና በሊጉ ካደረጋቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች መካከል ሁለቱን ሲያሸንፍ አራት ጊዜ ተሸንፏል። ሶስት ጊዜ ደግሞ አቻ መውጣት ችሏል። ስምንት ግቦችን ሲያስቆጥር 10 ጎሎችን አስተናግዷል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ሲዳማ ቡና በዘጠኝ ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል።
አካባቢ ጥበቃ
ረቂቅ አዋጁ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስራዎችን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ጉልህ ጠቀሜታ ይኖረዋል 
Dec 5, 2025 188
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 26/2018(ኢዜአ)፦የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ የሀገሪቱን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስራዎች የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ ገለጹ። በሕዝበ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት እና የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ይፋዊ ውይይት መድረክ አካሂደዋል።   በምክር ቤቱ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ በዚሁ ወቅት፤ የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ በተለያዩ አሰራሮች ላይ መኖሩን ጠቅሰዋል፡፡ አንድ ወጥ በሆነ አሰራር፣ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችና ሀገሪቱ ከደረሰችበት ደረጃ ጋር በተጣጣመ መልኩ ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱ አስፈላጊ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የሀገሪቱን የበለጸገ የስነ ምህዳር ሀብት ዘላቂ በሆነ ወጥ አሰራር ለማጠናከር የአገልግሎት ክፍያ ስርዓቱ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የደን ልማቶች የግብርና ምርታማነትን በማጎልበት አረንጓዴ ልማቶችን የበለጠ ውጤታማ ያደርጋል ብለዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የተፈጥሮ ሀብቶችን ጥበቃና እንክብካቤን በማጠናከር አካባቢ ላይ የሚደርሰውን ጉዳትና የህብረተሰቡን ተጋላጭነት መቀነስ አስፈላጊ ነው።   ረቂቅ አዋጁ ለመጀመሪያ ጊዜ መዘጋጀቱን ገልጸው፤ የተለያዩ ማህበረሰብ ክፍሎች አካባቢያቸውን በመጠበቃቸው ለአገልግሎታቸው ክፍያ እንዲያገኙ የሚያደርግ የማበረታቻ ስርዓት የሚዘረጋ ነው ብለዋል። ስነ ምህዳር ላይ ጉዳት የሚያደርሱ እንቅስቃሴዎችን ለመከላከል የአካባቢን ጥበቃ በዘላቂነት የሚያበረታታ ሂደትን የሚፈጥር አዋጅ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙ ባለ ድርሻ አካላት የስነ ምህዳር አገልግሎት አቅራቢዎች፣ ረቂቅ አዋጁ ላይ መካተት የሚገባቸውን ጉዳዮች፣ ግልጽነትን የሚጠይቁና ከትርጉም ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤በረቂቅ አዋጁ የስነ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ላይ የማህበረሰቡና የባለ ድርሻ አካላት ተጠቃሚነት፣ ተሳታፊነትና ፍትሃዊነት በግልጽ መቀመጡን ተናግረዋል። አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ የመንግስት ተቋማትና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት አገልግሎት አቅራቢዎች ይሆናሉ ብለዋል። ከግብርናና ከደን ልማት ጋር ተያይዞ የስነ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ አስገዳጅ የሆነባቸው አዋጆች መኖራቸውን ጠቅሰው ረቂቅ አዋጁ የክፍያ ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የፌደራልና የክልል ባለ ድርሻ አካላትን ሚና እና ሀላፊነትም በግልጽ አስቀምጧል ብለዋል።   በምክር ቤቱ የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር)፤ በረቂቅ አዋጁ ላይ አሻሚ ትርጉም የሚሰጡ፣ ግልጽነት የጎደላቸው ጉዳዮች ተሻሽለው ጠንካራ አዋጅ እንዲወጣ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።
በኢሉባቦር ዞን በክረምቱ ወቅት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ እየተከናወነ ነው
Dec 2, 2025 297
መቱ ፤ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፡-በኢሉባቦር ዞን በክረምቱ አረንጓዴ አሻራ መርሐግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በዘመቻ መልክ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የዞኑ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ሰራተኞች የተሳተፉበት በክረምቱ ወቅት የተተከሉ ችግኞችን በጋራ እየተንከባከቡ ናቸው። የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አወል መሐመድ በዞኑ በክረምቱ ወራት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰዋል። የችግኞቹን የጽድቀት መጠን ለማሳደግም ህብረተሰቡ እንክብካቤ እንዲያደርግ ግንዛቤ በመፈጠሩ የዞኑ የመንግስት ሰራኞችን ጨምሮ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍሎች ባሳተፈ መልኩ እንክብካቤው በዘመቻ መልክ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም የጽድቀት መጠናቸው በአሁኑ ወቅት ከ95 በመቶ በላይ መድረሱን ተናግረዋል። ለችግኞቹ የሚደረገው እንክብካቤ ጽድቀታቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ በአጭር ግዜ ደርሰው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው እንዲጎላ እንደሚያግዝም አመልክተዋል። በችግኝ እንክብካቤው ከተሳተፉ የመንግስት ሰራተኞች መካከል የዞኑ የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽሕፈት ቤት ባለሞያ አቶ መላኩ ከበደ በበኩላቸው በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአንድነት የተከልናቸውን ችግኞች በአንድነት የመንከባከብ ስራ እየሰራን ነው ብለዋል። በመንግስት አገልግሎት ለህዝብ ከሚሰጧቸው አገልግሎት ባለፈ በክረምቱ ወራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከሏቸውን ችግኞች በመንከባከብ እንዲጸድቁ ለማድረግ በስፍራው መገኘታቸውን ገልጸዋል። በአረንጓዴ አሻራ የተከልሏቸው ችግኞች የሚጠበቀውን ውጤት ለማግኘት መትከል ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የእንክብካቤ ስራውን ማጠናከር በማስፈለጉ ለዚሁ ተግባር መጥቻለሁ ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ፋጡማ የሱፍ ናቸው። አቶ እንዳሻው ጆቴ በበኩላቸው የተተከሉ ችግኞችን በጋራ በመንከባከብ ለውጤት ለማብቃት ያልተቋረጠ ክትትል በማስፈለጉ በተከላ ወቅቱ የገቡትን ቃል በተግባር ለማዋል ስራው ላይ መገኘታቸውን ጠቁመዋል። በክረምቱ የተተከሉት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተገቢው እንክብካቤ ካልተደረገላቸው በመጥፋት የወጣባቸው ከፍተኛ ገንዘብ ለብክነት እንደሚዳረግም አክለዋል።  
ኢትዮጵያውያን የደመቁበት የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ
Dec 1, 2025 307
ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ ተከናውኗል። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ የሽልማት መርሃ ግብሩ የሚዲያ አጋር ሲሆን የሁለት ቀኑን የሽልማት መርሃ ግብር የቀጥታ ስርጭት ሽፋን በመስጠት ለመላው አፍሪካውያን ተደራሽ አድርጓል። የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ(አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ አድርጓል። የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያን ጎብኝተዋል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች ተከናውኗል። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ያስገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ከ94ቱ ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ሶስቱ በተለያዩ ዘርፎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ አሸናፊ በመሆን ሽልማቱን ተቀብሏል። ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ ሽልማቱን የተጎናጸፈው “Climate Intelligence for Survival: IGAD’s Push for Accurate, Actionable Data” በሚል ርዕስ በጻፈው ጽሁፍ ነው። የጋዜጠኛ ጌትነት ጽሁፍ በኢጋድ ቀጣና ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና የሚዳስስ ነው። በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰት ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋዎችና ኢ-ተገማች የአየር ጸባይ ለውጦች ዜጎችን በማፈናቀል እና በቁም እንስሳት ላይ ያደረሱትን ጉዳት ይቃኛል። ትክክለኛ፣ ጊዜውን የጠበቀና ለተግባር ምላሽ የሚያገለግሉ የአየር ንብረት መረጃዎች የማይበገር አቅም ለመገንባትና አደጋዎችን ለመከላከል ያላቸውን ሚናም ተዳሷል። በጽሁፉ ላይ የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያና ትግበራ ማዕከል(ICPAC) የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን በማጠናከር፣ የትንበያ አቅም ማሳደግና የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት የመቋቋም አቅም ላይ እያከናወነ ያለው ስራ ተቀምጧል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች፣ የአንበጣ መንጋ፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብና ሌሎች ፈተናዎችን ለመከላከል ተአማኒነት ያለው የአየር ንብረት መረጃ ወሳኝ መሆኑም ተመላክቷል። በተለይም ኑሯቸው በተለያዩ ወቅቶች ላይ ለተመረኮዙ አርሶ እና አርብቶ አደሮች መረጃው ወሳኝ መሆኑን ያስቀምጣል። ሌላኛው ተሸላሚ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤ) ጋዜጠኛ ሽመክት ጉግሳ ነው። የተሸለመበት ዘርፍ በኦሮምኛ ቋንቋ በሰራው ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሙ ዛፎች ከሰው ህይወት ጋር ያላቸውን ቁርኝት በዋናነት ይቃኛል። መንደርደሪያውን ከዓለም የዛፍ ጠቀሜታና ጥበቃ በማድረግ በኦሮሚያ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ይዳስሳል። ዛፍ መትከል ተፈጥሮና የሰው ልጅን እንዴት እንደሚጠብቅ በተቃራኒው መቁረጥ የሚያደርሰውን ጉዳትም ያስቃኛል። የ21 ደቂቃ ፕሮግራሙ የኦሮሞ ህዝብ በዘመናት መካከል ዛፎችና የደን ሀብቶች እንዲጠበቁ ያደረገው አስተዋጽኦ ተወስቶበታል። በተለይም በገዳ ስርዓት ውስጥ ዛፍን መጠበቅ ያለው ሚና በስፋት ተነስቷል። አንድ ዛፍ ለአራት ሰዎች መኖር መሠረት ይሆናል፤ ዛፍ መቁረጥ አራት ሰዎችን እንዲሞቱ ያደርጋል የሚል የአባገዳ አስተያየትም ተጠቃሽ ነው። አባ ገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ እናቶችና የአካባቢ ማህበረሰቦች ተፈጥሮን ጠብቆ በማቆየት ያላቸው ሚና ቁልፍ እንደሆነ ተመላክቷል። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መስራችና ስራ አስኪያጅ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተበርክቶላታል። ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በሬዲዮ ጋዜጠኝነት ግንባር ቀደምና በዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቷንም ኢጋድ ገልጿል። በብሮድካስት ሚዲያው ከ40 ዓመት በላይ የቆየችው ጋዜጠኛ መዓዛ ሸገር ኤፍኤም 102.1ን ከ18 ዓመታት በፊት በማቋቋም በኢትዮጵያ ቀዳሚ የመረጃ እና የመዝናኛ ጣቢያ እንዲሆን ማድረጓ አመልክቷል። ከጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ አበይት ፕሮግራሞች መካከል “ማንን ምን እንጠይቅልዎ?” እና “ሸገር ካፌ” ተጠቃሽ ናቸው። ጋዜጠኛዋ በፕሮግራሞቹ ህዝብን ከመንግስት አገልግሎቶች ጋር በማገናኘትና በማህበራዊ፣ የህግ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ላይ የተመረኮዙ ውይይቶች እንዲካሄዱ መድረክ መፍጠር መቻሏንም ነው የገለጸው። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መሪ ሀሳብ በሆነው የእናንተ ሬዲዮ መዓዛ በጋዜጠኝነት ሙያ ህዝብን ለማገልገልና የኢትዮጵያውያንን ድምጽ ለማጉላት ያላትን ቁርጠኝነት ኢጋድ አድንቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ኢጋድ አመልክቷል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 1, 2025 291
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንደገለፀው በሚቀጥሉት አሥር ቀናት ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት አካባቢዎች ላይ ቀጣይነት ይኖረዋል። ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጥቂት የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናቶች ላይ በተዳከመ ሁኔታ ቀጣይነት ይኖራቸዋል። በዚህም የደቡብ ኦሮሚያ ዞኖች፤ የሲዳማ ክልል ዞኖች፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡባዊ ዞኖች እና የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ዞኖች በጥቂት ስፍራዎቻቸው ላይ በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙ ገልጿል። በሌላ በኩል ከሚኖረው የደመና ሽፋን ላይ በመነሳት በጥቂት የሰሜን፣ መካከለኛውና ደቡብ ጎንደር ዞኖች፣ ባህርዳር ዙሪያ፣ አዊ ፣ በምዕራብና ምስራቅ ጎጃም አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናት ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ትንበያው አብራርቷል። የምዕራብ ኦሮሚያ ክልል ዞኖች፣ አርሲ እና ምዕራብ አርሲ፤ ባሌ እና ምስራቅ ባሌ ዞኖች፣ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ እና የማኦኮሞ ልዩ ዞን፤ የጋምቤላ ክልል ዞኖች፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዞኖችም አልፎ አልፎ ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ። ስለሆነም በሚኖሩት ደረቅ ቀናቶች የደረሱ ሰብሎች መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል። በሌላ በኩል ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩም በመግለጫው ተብራርቷል። በዚህም የበጋው ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በተለይም በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መካከለኛውና ደቡብ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የለሊትና የማለዳው ቅዝቃዜ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን ትንበያው ያሳያል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 285
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል።   በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው።   አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 325
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 681
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 572
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ሐተታዎች
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 496
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 730
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 758
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 803
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2802
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2751
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3647
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3727
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2045
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1337
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7155
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5642
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57794
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52603
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33289
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30812
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26701
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25436
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25014
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25001
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57794
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52603
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33289
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30812
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 470
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው።   እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም።   የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል።   የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል።   ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!
ብልህ ከችግር ይማራል!!
Dec 2, 2025 313
ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል!! በማሙሽ ጋረደው ገራድ ተስፋዬ ተፈራ ትውልድና እድገታቸው በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ቃልሻ ቀበሌ ሲሆን በ1999 ዓ.ም በህገ ወጥ መንገድ ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው እንደነበር ያስታውሳሉ። ገንዘብ ለማግኘትና የመለውጥ ህልማቸውን ለማሳካት በሚል ሩቅ አስበው የጀመሩት ህገ ወጥ ጉዞ መዳረሻውን እስር ቤት አደረገው። ይህም ሁኔታ ''ሩቅ አሳቢ-ቅርብ አዳሪ'' አደረጋቸው። በባዕድ አገር በነበራቸው የ2 ዓመት የእስር ቤት ቆይታም የምግብ እጦትን ጨምሮ አካላዊ ጥቃትና ጉልበት ብዝበዛ እንዲሁም የተለያዩ ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶችን እንዳስተናገዱ ይናገራሉ።   ይህም አልበቃ ብሎ ከአካባቢው በህገወጥ መንገድ የሚሰደዱ ወጣቶችን ጉልበት በመጠቀም ሰፋፊ እርሻዎች ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ የጉልበት ብዝበዛ ይፈፀምባቸው እንደነበርም ያስታውሳሉ። ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል! የሚሉት ገራድ ተስፋዬ ሩቅ ሳይጓዙ፣ ገንዘብ ሳያወጡ ሰርተው መለወጥ የሚችሉበትን አካባቢያቸውን ፀጋ ሳያማትሩ ስደት መሄዳቸው ቁጭት ፈጥሮባቸው ነበር፡፡ ይህም በሀገራቸው እንኳንስ የለማን መሬት ይቅርና የተቦረቦረ መሬትን አልምቶ ጉልበትንና ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል ከእስር ቤት ቆይታቸው ተምረው ከእስር እንደተፈቱም ወዲያውኑ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል። በ2001 ዓ.ም ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሱም በማህበር ተደራጅተው ከመንግሥት ባገኙት 70 ሺህ ብር ብድር በእንስሳት እርባታ ላይ ለመሰማራት 4 የወተት ከብቶችን ገዝተው የእርባታ ስራ መጀመራቸውን ይገልጻሉ፡፡   በዚህም የዞኑ አስተዳደር የሰጣቸውን መሬት አልምተው የእንስሳት እርባታውን አስፋፍተው መስራት ጀመሩ፡፡ አሁን ላይ የወተት ላሞቹን ቁጥር 37 በማድረስ የወተት ምርታማነታቸው አድጎ ከቤት ፍጆታ አልፎ ለሆሳዕና ከተማና አካባቢው በቀን ከ670 ሊትር በላይ ወተት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ለ40 ወጣቶችም ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ከመፍጠራቸውም ባሻገር የተለያዩ የጭነትና የስራ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራት መቻላቸውን ይናገራሉ። የጀመሩትን ስራ በጥምር ግብርና የማስፋትና የሚያገኙትን ወተት በማቀነባበር ምርቱን በተለያየ መልኩ ለገበያ የማቅረብ ራዕይን ሰንቀው በትጋት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በህገወጥ ስደት ካጋጠማቸው ችግር ተነስተው በተግባር ያዩትን ለሌሎች በማስተማር የስደትን አስከፊነት ለአካባቢያቸው ወጣቶች እያስገነዘቡ መሆኑን ገልጸዋል።   ወጣቶች የስደትን አማራጭ ከመመልከታቸው በፊት የአካባቢያቸውን ፀጋ እንዲቃኙና ራዕይ ሰንቀው ራሳቸውን ለማሻሻል እንዲሰሩም መክረዋል። መለወጥ በውጪ ሀገር ብቻ ያለ የሚመስላቸው የቤተሰብ ኃላፊዎችም ልጆቻቸው በሀገራቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ በማመን ሊያግዟቸው እንደሚገባም አቶ ገራድ አስገንዝበዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደስላሴ፤ በክልሉ በርካታ ወጣቶች ያልተጨበጠ ተስፋ ሰንቀው ለህገወጥ ስደትና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡   በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ የሚያስችል አቅም በግብርናው ዘርፍ መኖሩን ጠቅሰው በዘርፉ የተሰማሩ ከስደት ተመላሾች በአካባቢያቸው ሰርተው ለስኬት እየበቁ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ላይ የሚገኙና የእነዚህን አካላት ተሞክሮ በመውሰድ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም