ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የመረጃ ስርዓቱ ሳይንሳዊ መንገዶችን በመከተል አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው
May 9, 2026 25
ሰመራ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ብሔራዊ የግጦሽ መሬት የጤና ክትትል የመረጃ ስርዓት ሳይንሳዊ መንገዶችን በመከተል አርብቶ አደሩን እና ከፊል አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገለጸ። በአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች ተግባራዊ የሚደረግ ብሔራዊ የግጦሽ መሬት የጤና ክትትል የመረጃ ስርዓት ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ዛሬ በሰመራ ተካሄዷል። በመድረኩም ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ዑመር ኑሩ እንደገለፁት፤ በክልሉ የአርብቶ አደሩንና ከፊል አርብቶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባራት ይጠናከራሉ።   የአርብቶ አደሩ ህይወት ከእንስሳት ሀብቱና ከግጦሽ መሬቱ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ መሆኑን አውስተው የመረጃ ስርዓቱ ሳይንሳዊ መንገዶችን በመከተል አርብቶ አደሩን እና ከፊል አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ እንደሚያደርገው ገልጸዋል። የመረጃ ስርዓቱ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በመሬት መራቆትና በመጤ አረሞች ምክንያት ጉዳት ለደረሰበት መሬት መፍትሄን ይዞ የመጣ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑንም አክለዋል። በተለይም የአዋሽ ወንዝን ተከትሎ በርካታ አካባቢዎች በመጤ አረም በመወረራቸው ሳቢያ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን ጠቁመው ችግሩን ለመቅረፍም ሳይንሳዊ ዘዴን በመጠቀም ጥረት መደረጉ የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ያሳድገዋል ብለዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የእንስሳትና ንግድ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዮሴፍ መካሻ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመረጃ ስርዓቱ በተለይም ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ነው ብለዋል።   በተጨማሪም ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለትምህርት ተቋማትና ሌሎች አካላት መረጃ በመስጠት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ እገዛ እንደሚያደርግም አክለዋል። ስርዓቱ ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ለግጦሽ የሚውሉ ስፍራዎችን በመለየት፣ የተራቆቱና ጉዳት የደረሰባቸው እንዲታወቁ አስፈላጊውን መረጃ በማድረስ ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም መሐመድ ናቸው።   ይህም በክልሉ ያለውን የዘርፉን አቅምና ክፍተት በመለየት ለምርታማነት መጨመር ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም አክለዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ የትውልድን የተሻለ መፃኢ እጣ ፋንታ የሚወስን ወሳኝ መድረክ ነው
May 9, 2026 63
አዲስ አበባ ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የትውልድን የተሻለ መፃኢ እጣ ፋንታ የሚወስን ወሳኝ የጋራ መድረክ መሆኑ ተገለጸ። ወጣቶች በሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ ሀገራዊ መግባባትን በሚፈጥሩ የመፍትሔ ሃሳቦች ላይ ግንባር ቀደም ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባም መልዕክት አስተላልፈዋል። በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ የልዩነት ሃሳቦችን በምክክር በመፍታት በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ትውልድ ለመፍጠር ሀገራዊ ምክክር አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል። በሁሉም ክልሎች፣ በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ከሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችና አደረጃጀቶች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ በስኬት ተጠናቋል። በዚህም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ማጠናቀቁን ተከትሎ ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል። የክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ምክክሩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን በማስፈን ዘላቂ ሰላምና አንድነትን ለማምጣት ወሳኝ መድረክ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የፈጠረውን ዕድልም በታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና መሰል ጉዳዮች በሚስተዋሉ ዋና ዋና ሀገራዊ የሃሳብ ልዩነቶች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽነር ማርቆስ ማቲዎስ፤ ሀገራዊ ምክክር ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንቢያ መሳሪያ ነው ብለዋል። ወጣቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችም ሀገራዊ ምክክር የፈጠረውን ዕድል በመጠቀም የኢትዮጵያን መፃኢ እጣፋንታ የተሻለ ለማድረግ በትብብር መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሱልጣን አሊ፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የትውልድን መፃኢ እጣ ፋንታ የሚወስን ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል። በዚህም በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሂደት ወጣቶች ከፍተኛ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል። በቀጣይም ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሚካሄድበት ወቅት ወጣቶች ገንቢ ሚና እንዲወጡ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማኅበር አባል በቃሉ መሰረት፤ በክልሉ የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎች ላይ በንቃት መሳተፋቸውን አስታውሷል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርም በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጿል። በቀጣይም ዋናውን ሀገራዊ ምክክር በማካሄድ ሂደት ገንቢ ሚና እንደሚወጡ ተናግረዋል።
የሚታይ
የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በተግባር የሚለካ ውጤት የተገኘባቸው ናቸው
May 9, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በተግባር የሚለካ ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በስድስት ክፍለ ከተሞች ግንባታቸው የተጠናቀቁ የብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሕንፃዎችን መርቀዋል።   በዚሁ ወቅት እንዳሉትም፤ ግንባታቸው ተጠናቆ የተመረቁ የብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሕንፃዎች የጋራ ትርክት በማስረፅ ሕብረብሔራዊ አንድነት የሚጠናከርባቸው ናቸው። የኢትዮጵያ ብልፅግና በማረጋገጥ የሀገረ መንግስት ግንባታ የሚጠናከርባቸውና ጀምሮ የማጠናቀቅ ልምምድ ዕድገት ወሳኝ ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ዓመታት ፈተናን ወደ ድል በመቀየር በሁሉም መስክ አመርቂ የልማት ውጤቶች የተመዘገቡባቸው መሆናቸውን ተናግረዋል። አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ በተያዘው ግብ መሠረትም በመዲናዋ በሁሉም መስክ ስምና ገፅታዋን የሚመጥን የልማት ሥራ መሰራቱን አንስተዋል። የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶችም የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በተግባር የሚለካ አመርቂ ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን አስረድተዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን ህብረብሄራዊ አንድነትና የጋራ ትርክት በማጠናከር ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በትጋት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ፓርቲው ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን በማጠናከር የታለመውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ይሰራል
May 9, 2026 84
ጋምቤላ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን በማጠናከር የታለመውን ብልጽግና እውን ለማድረግ እንደሚሰራ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። ፓርቲው "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ አባላቱና ደጋፊዎቹ በተገኙበት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ዓለሚቱ ኡሞድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በመደመር እሳቤ ባለፉት ዓመታት እንደ ክልል ብሎም እንደ ሀገር በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ የልማት ድሎች ተመዝግበዋል።   ባለፉት ዓመታት ፓርቲው ለህዝብ በገበው ቃል መሰረት በተለይ ለህዝብ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ በመስጠት በኩል ውጤታማ ሥራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲው የህዝብ ይሁንታ ካገኘ የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል የታለመውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። ፓርቲው በመደመር እሳቤ በህዝቦች መካከል ያለውን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት ይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ አበክሮ እንደሚሰራም ነው ያረጋገጡት።   ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር ላቀዳቸው የልማት ግቦች መሳካት ህዝቡ ከፓርቲው ጎን በመሆን በጠቅላላ ምርጫው ይሁንታውን እንዲሰጠውም ጥሪ አቅርበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን በበኩላቸው ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ዘላቂ ልማት እውን ለማድረግ ያለመታከት እየሰራ ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በየአካባቢው የሚገኙ ጸጋዎችን ካለው የሰው ኃይል ጋር አቀናጅቶ ባከናወናቸው የልማት ሥራዎች በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።
የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በሕዝብ ይሁንታ ድምጽ ለማግኘት ዝግጅት አድርጓል - የፓርቲው ፕሬዝዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር)
May 9, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በመጪው ሀገራዊ ምርጫ በሕዝብ ይሁንታ ድምጽ ለማግኘት ዝግጅት ማድረጉን የፓርቲው ፕሬዚዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር) ገልጹ። የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ያለውን አማራጭ የፖሊሲ ሃሳቦች ለህዝብ ለማስተዋወቅ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ መርሃ ግብር ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። ፓርቲው ባካሄደው የቅስቀሳ መርሃ ግብር በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በፖለቲካዊ ዘርፎች የያዛቸውን አዳዲስ አማራጭ ዕቅዶች ለደጋፊዎቹና ለነዋሪው አቅርቧል። የፓርቲው ፕሬዚዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር) በወቅቱ፤ ፓርቲያቸው ተፎካክሮ መንግስት መሆን የሚያስችለውን ድምጽ ለማግኘት ሁለንተናዊ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው ‎የተለያዩ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ቀርጾ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ አመልክተው፤ ባለፉት ቀናት በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ዓላማውን ለህዝብ ሲያስተዋውቅ መቆየቱን ተናግረዋል። የዛሬው የአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ቅስቀሳ ፓርቲው ያለውን የፖሊሲ አማራጭ ለነዋሪው በቀጥታ ለማድረስና የምረጡኝ ጥሪ ለማቅረብ የታለመ ነው ብለዋል። ‎በሀገሪቱ እየተገነባ ያለውን የዴሞክራሲ ስርዓት ለማጠናከር የፖለቲካ ፓርቲዎች በነጻነት መንቀሳቀሳቸውና ሃሳባቸውን ለህዝብ ማቅረባቸው ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ የዛሬው መርሃ ግብርም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው የምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን አመልክተው፤ በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ‎የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው የምርጫ ምልክቱ ብዕር ማድረጉንና የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገባ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ፖሊሲ አዘጋጅቷል ብለዋል። ፓርቲው አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎችና ከተሞች ፖሊሲውን በተለያዩ መንገዶች እያስተዋወቀ መሆኑን አመልክተዋል። ፓርቲው የተፈጠረውን ምቹ የምርጫ ሁኔታ በመጠቀምና በተለያዩ መንገዶች ለደጋፊዎቹና ለመላው የሀገሪቱ ሕዝቦች አማራጭ የፖሊሲ ሀሳቦቹን እያስተዋወቀ መሆኑን የገለጹት የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ አዲስ መሐመድ ናቸው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ሚና ይወጣል
May 9, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ገንቢ ሚና እንደሚወጣ የፓርቲው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት፣ በሀገራዊና ቀጣናዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። መድረኩን አስመልክቶ የፓርቲው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የሀገር ዘላቂ ልማትና ሰላም የፓርቲው ቀዳሚ አጀንዳዎች ናቸው ብለዋል። የአንድ ሀገር ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነትም ዘላቂ ልማትና ሰላምን በማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያፀና መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።   በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኅን አማራጮችን በመጠቀም የፖሊሲ አማራጫቸውን እያስተዋወቁ እንደሚገኙም ተናግረዋል። በመድረኩም በምርጫ ዝግጅት ምዕራፍ የፖሊሲ አማራጮች ታትመው በዛሬው ዕለት ለመድረክ ተሳታፊዎች አንደሚታደል አስታውቀዋል። በመድረኩ በምርጫ እና ድህረ ምርጫ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሀሳቦች እና የፓርቲው ሚና ምን መሆን እንዳለበት ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትና ከዕጩ ተወዳዳሪዎች ጋር ውይይት ይደረጋል ብለዋል። ፓርቲው ለሰላም፣ ለልማትና ቀጣይነት ላለው ሀገራዊ ዕድገት የሚጠበቅበትን ገንቢ ሚና እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲያቸው ለምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚወጣ አንስተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በሕብረ ብሔራዊ አንድነት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ  
May 9, 2026 63
ቆሼ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦በሕብረ ብሔራዊ አንድነት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ብልጽግና ፓርቲ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳውን በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ አካሂዷል።   በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በፓርቲው በመደመር እሳቤ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተጀመረውን የብልጽግናና የማንሰራራት ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በተሰሩ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። በፖለቲካ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲውና በሌሎች መስኮች በተከናወኑ ሥራዎች በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ስለመቻሉም አመልክተዋል። ፓርቲው አስተሳሳሪ ትርክትን በመገንባት፣ በአካባቢው ሰላምን በማጠናከርና በሁሉም ዘርፍ ውጤታማነትን በማሳደግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እያሳደገ መምጣቱንም ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ በፓርቲው መሪነት የማህበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አመልክተዋል፡፡   የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ በበኩላቸው፤ በለውጡ መንግስት የልዩ ወረዳው ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር የዘመናት ጥያቄው ምላሽ ማግኘቱን ተናግረዋል። በዚህም ህብረተሰቡ ከልማት ትሩፋት ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመሆን ተሳትፎውን ማጠናከር አለበት ብለዋል። በቅስቀሳ መርሃ ግብሩ ላይ የክልል፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን እና የልዩ ወረዳው ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ፓርቲው ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን በማጠናከር የታለመውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ይሰራል
May 9, 2026 84
ጋምቤላ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን በማጠናከር የታለመውን ብልጽግና እውን ለማድረግ እንደሚሰራ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። ፓርቲው "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ አባላቱና ደጋፊዎቹ በተገኙበት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ዓለሚቱ ኡሞድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በመደመር እሳቤ ባለፉት ዓመታት እንደ ክልል ብሎም እንደ ሀገር በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ የልማት ድሎች ተመዝግበዋል።   ባለፉት ዓመታት ፓርቲው ለህዝብ በገበው ቃል መሰረት በተለይ ለህዝብ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ በመስጠት በኩል ውጤታማ ሥራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲው የህዝብ ይሁንታ ካገኘ የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል የታለመውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። ፓርቲው በመደመር እሳቤ በህዝቦች መካከል ያለውን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት ይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ አበክሮ እንደሚሰራም ነው ያረጋገጡት።   ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር ላቀዳቸው የልማት ግቦች መሳካት ህዝቡ ከፓርቲው ጎን በመሆን በጠቅላላ ምርጫው ይሁንታውን እንዲሰጠውም ጥሪ አቅርበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን በበኩላቸው ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ዘላቂ ልማት እውን ለማድረግ ያለመታከት እየሰራ ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በየአካባቢው የሚገኙ ጸጋዎችን ካለው የሰው ኃይል ጋር አቀናጅቶ ባከናወናቸው የልማት ሥራዎች በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።
የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በሕዝብ ይሁንታ ድምጽ ለማግኘት ዝግጅት አድርጓል - የፓርቲው ፕሬዝዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር)
May 9, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በመጪው ሀገራዊ ምርጫ በሕዝብ ይሁንታ ድምጽ ለማግኘት ዝግጅት ማድረጉን የፓርቲው ፕሬዚዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር) ገልጹ። የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ያለውን አማራጭ የፖሊሲ ሃሳቦች ለህዝብ ለማስተዋወቅ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ መርሃ ግብር ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። ፓርቲው ባካሄደው የቅስቀሳ መርሃ ግብር በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በፖለቲካዊ ዘርፎች የያዛቸውን አዳዲስ አማራጭ ዕቅዶች ለደጋፊዎቹና ለነዋሪው አቅርቧል። የፓርቲው ፕሬዚዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር) በወቅቱ፤ ፓርቲያቸው ተፎካክሮ መንግስት መሆን የሚያስችለውን ድምጽ ለማግኘት ሁለንተናዊ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው ‎የተለያዩ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ቀርጾ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ አመልክተው፤ ባለፉት ቀናት በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ዓላማውን ለህዝብ ሲያስተዋውቅ መቆየቱን ተናግረዋል። የዛሬው የአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ቅስቀሳ ፓርቲው ያለውን የፖሊሲ አማራጭ ለነዋሪው በቀጥታ ለማድረስና የምረጡኝ ጥሪ ለማቅረብ የታለመ ነው ብለዋል። ‎በሀገሪቱ እየተገነባ ያለውን የዴሞክራሲ ስርዓት ለማጠናከር የፖለቲካ ፓርቲዎች በነጻነት መንቀሳቀሳቸውና ሃሳባቸውን ለህዝብ ማቅረባቸው ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ የዛሬው መርሃ ግብርም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው የምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን አመልክተው፤ በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ‎የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው የምርጫ ምልክቱ ብዕር ማድረጉንና የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገባ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ፖሊሲ አዘጋጅቷል ብለዋል። ፓርቲው አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎችና ከተሞች ፖሊሲውን በተለያዩ መንገዶች እያስተዋወቀ መሆኑን አመልክተዋል። ፓርቲው የተፈጠረውን ምቹ የምርጫ ሁኔታ በመጠቀምና በተለያዩ መንገዶች ለደጋፊዎቹና ለመላው የሀገሪቱ ሕዝቦች አማራጭ የፖሊሲ ሀሳቦቹን እያስተዋወቀ መሆኑን የገለጹት የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ አዲስ መሐመድ ናቸው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ሚና ይወጣል
May 9, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ገንቢ ሚና እንደሚወጣ የፓርቲው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት፣ በሀገራዊና ቀጣናዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። መድረኩን አስመልክቶ የፓርቲው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የሀገር ዘላቂ ልማትና ሰላም የፓርቲው ቀዳሚ አጀንዳዎች ናቸው ብለዋል። የአንድ ሀገር ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነትም ዘላቂ ልማትና ሰላምን በማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያፀና መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።   በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኅን አማራጮችን በመጠቀም የፖሊሲ አማራጫቸውን እያስተዋወቁ እንደሚገኙም ተናግረዋል። በመድረኩም በምርጫ ዝግጅት ምዕራፍ የፖሊሲ አማራጮች ታትመው በዛሬው ዕለት ለመድረክ ተሳታፊዎች አንደሚታደል አስታውቀዋል። በመድረኩ በምርጫ እና ድህረ ምርጫ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሀሳቦች እና የፓርቲው ሚና ምን መሆን እንዳለበት ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትና ከዕጩ ተወዳዳሪዎች ጋር ውይይት ይደረጋል ብለዋል። ፓርቲው ለሰላም፣ ለልማትና ቀጣይነት ላለው ሀገራዊ ዕድገት የሚጠበቅበትን ገንቢ ሚና እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲያቸው ለምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚወጣ አንስተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል።
በአቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የአፍሪካ ህብረት እና የኮሜሳ የጋራ ልዑክ በዛምቢያ የቅድመ ምርጫ ምልከታ አከናወነ
May 9, 2026 85
አዲስ አበባ ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በአቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የአፍሪካ ህብረት እና የኮሜሳ የጋራ ልዑክ በዛምቢያ የቅድመ ምርጫ ምልከታ አከናውኗል። የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ ከሚያዝያ 26 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በዛምቢያ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። በቆይታቸውም ነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው የዛምቢያ አጠቃላይ ምርጫ አስቀድሞ የተሰየመውን የአፍሪካ ህብረት እና የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የጋራ የቅድመ ምርጫ እና የፍላጎት ግምገማ ልዑክን በሊቀመንበርነት መርተዋል። አቶ ደመቀ መኮንን እና ከአፍሪካ ህብረት እንዲሁም ከኮሜሳ የተውጣጣው ልዑክ ከምርጫ እና የመልካም አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክሮችን አድርገዋል። በውይይቶቹ የዛምቢያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለምአቀፍ ትብብር ሚኒስቴር፣ የዛምቢያ ምርጫ ኮሚሽን፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች፣ የኮሜሳ ዋና ፀሐፊ፣ የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል። ምክክሩ በዋናነት በዛምቢያ ያለውን የቅድመ ምርጫ ድባብ እንዲሁም የምርጫ አስፈጻሚ ተቋማትን ዝግጁነት በመፈተሽ ላይ ያተኮረ ነው። በተጨማሪም ነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒ፣ ግልጽ እና አካታች እንዲሆን እየተከናወኑ ባሉ ጥረቶች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ፖለቲካ
በሕብረ ብሔራዊ አንድነት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ  
May 9, 2026 63
ቆሼ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦በሕብረ ብሔራዊ አንድነት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ብልጽግና ፓርቲ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳውን በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ አካሂዷል።   በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በፓርቲው በመደመር እሳቤ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተጀመረውን የብልጽግናና የማንሰራራት ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በተሰሩ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። በፖለቲካ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲውና በሌሎች መስኮች በተከናወኑ ሥራዎች በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ስለመቻሉም አመልክተዋል። ፓርቲው አስተሳሳሪ ትርክትን በመገንባት፣ በአካባቢው ሰላምን በማጠናከርና በሁሉም ዘርፍ ውጤታማነትን በማሳደግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እያሳደገ መምጣቱንም ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ በፓርቲው መሪነት የማህበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አመልክተዋል፡፡   የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ በበኩላቸው፤ በለውጡ መንግስት የልዩ ወረዳው ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር የዘመናት ጥያቄው ምላሽ ማግኘቱን ተናግረዋል። በዚህም ህብረተሰቡ ከልማት ትሩፋት ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመሆን ተሳትፎውን ማጠናከር አለበት ብለዋል። በቅስቀሳ መርሃ ግብሩ ላይ የክልል፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን እና የልዩ ወረዳው ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ፓርቲው ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን በማጠናከር የታለመውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ይሰራል
May 9, 2026 84
ጋምቤላ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን በማጠናከር የታለመውን ብልጽግና እውን ለማድረግ እንደሚሰራ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። ፓርቲው "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ አባላቱና ደጋፊዎቹ በተገኙበት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ዓለሚቱ ኡሞድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በመደመር እሳቤ ባለፉት ዓመታት እንደ ክልል ብሎም እንደ ሀገር በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ የልማት ድሎች ተመዝግበዋል።   ባለፉት ዓመታት ፓርቲው ለህዝብ በገበው ቃል መሰረት በተለይ ለህዝብ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ በመስጠት በኩል ውጤታማ ሥራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲው የህዝብ ይሁንታ ካገኘ የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል የታለመውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። ፓርቲው በመደመር እሳቤ በህዝቦች መካከል ያለውን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት ይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ አበክሮ እንደሚሰራም ነው ያረጋገጡት።   ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር ላቀዳቸው የልማት ግቦች መሳካት ህዝቡ ከፓርቲው ጎን በመሆን በጠቅላላ ምርጫው ይሁንታውን እንዲሰጠውም ጥሪ አቅርበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን በበኩላቸው ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ዘላቂ ልማት እውን ለማድረግ ያለመታከት እየሰራ ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በየአካባቢው የሚገኙ ጸጋዎችን ካለው የሰው ኃይል ጋር አቀናጅቶ ባከናወናቸው የልማት ሥራዎች በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።
የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በሕዝብ ይሁንታ ድምጽ ለማግኘት ዝግጅት አድርጓል - የፓርቲው ፕሬዝዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር)
May 9, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በመጪው ሀገራዊ ምርጫ በሕዝብ ይሁንታ ድምጽ ለማግኘት ዝግጅት ማድረጉን የፓርቲው ፕሬዚዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር) ገልጹ። የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ያለውን አማራጭ የፖሊሲ ሃሳቦች ለህዝብ ለማስተዋወቅ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ መርሃ ግብር ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። ፓርቲው ባካሄደው የቅስቀሳ መርሃ ግብር በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በፖለቲካዊ ዘርፎች የያዛቸውን አዳዲስ አማራጭ ዕቅዶች ለደጋፊዎቹና ለነዋሪው አቅርቧል። የፓርቲው ፕሬዚዳንት አብዱልቃድር አደም (ዶ/ር) በወቅቱ፤ ፓርቲያቸው ተፎካክሮ መንግስት መሆን የሚያስችለውን ድምጽ ለማግኘት ሁለንተናዊ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው ‎የተለያዩ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ቀርጾ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ አመልክተው፤ ባለፉት ቀናት በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ዓላማውን ለህዝብ ሲያስተዋውቅ መቆየቱን ተናግረዋል። የዛሬው የአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ቅስቀሳ ፓርቲው ያለውን የፖሊሲ አማራጭ ለነዋሪው በቀጥታ ለማድረስና የምረጡኝ ጥሪ ለማቅረብ የታለመ ነው ብለዋል። ‎በሀገሪቱ እየተገነባ ያለውን የዴሞክራሲ ስርዓት ለማጠናከር የፖለቲካ ፓርቲዎች በነጻነት መንቀሳቀሳቸውና ሃሳባቸውን ለህዝብ ማቅረባቸው ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ የዛሬው መርሃ ግብርም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው የምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን አመልክተው፤ በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ‎የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው የምርጫ ምልክቱ ብዕር ማድረጉንና የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገባ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ፖሊሲ አዘጋጅቷል ብለዋል። ፓርቲው አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎችና ከተሞች ፖሊሲውን በተለያዩ መንገዶች እያስተዋወቀ መሆኑን አመልክተዋል። ፓርቲው የተፈጠረውን ምቹ የምርጫ ሁኔታ በመጠቀምና በተለያዩ መንገዶች ለደጋፊዎቹና ለመላው የሀገሪቱ ሕዝቦች አማራጭ የፖሊሲ ሀሳቦቹን እያስተዋወቀ መሆኑን የገለጹት የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ አዲስ መሐመድ ናቸው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ሚና ይወጣል
May 9, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ገንቢ ሚና እንደሚወጣ የፓርቲው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት፣ በሀገራዊና ቀጣናዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። መድረኩን አስመልክቶ የፓርቲው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የሀገር ዘላቂ ልማትና ሰላም የፓርቲው ቀዳሚ አጀንዳዎች ናቸው ብለዋል። የአንድ ሀገር ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነትም ዘላቂ ልማትና ሰላምን በማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያፀና መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።   በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኅን አማራጮችን በመጠቀም የፖሊሲ አማራጫቸውን እያስተዋወቁ እንደሚገኙም ተናግረዋል። በመድረኩም በምርጫ ዝግጅት ምዕራፍ የፖሊሲ አማራጮች ታትመው በዛሬው ዕለት ለመድረክ ተሳታፊዎች አንደሚታደል አስታውቀዋል። በመድረኩ በምርጫ እና ድህረ ምርጫ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሀሳቦች እና የፓርቲው ሚና ምን መሆን እንዳለበት ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትና ከዕጩ ተወዳዳሪዎች ጋር ውይይት ይደረጋል ብለዋል። ፓርቲው ለሰላም፣ ለልማትና ቀጣይነት ላለው ሀገራዊ ዕድገት የሚጠበቅበትን ገንቢ ሚና እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲያቸው ለምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊነት የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚወጣ አንስተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል።
በአቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የአፍሪካ ህብረት እና የኮሜሳ የጋራ ልዑክ በዛምቢያ የቅድመ ምርጫ ምልከታ አከናወነ
May 9, 2026 85
አዲስ አበባ ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በአቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የአፍሪካ ህብረት እና የኮሜሳ የጋራ ልዑክ በዛምቢያ የቅድመ ምርጫ ምልከታ አከናውኗል። የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ ከሚያዝያ 26 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በዛምቢያ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። በቆይታቸውም ነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው የዛምቢያ አጠቃላይ ምርጫ አስቀድሞ የተሰየመውን የአፍሪካ ህብረት እና የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የጋራ የቅድመ ምርጫ እና የፍላጎት ግምገማ ልዑክን በሊቀመንበርነት መርተዋል። አቶ ደመቀ መኮንን እና ከአፍሪካ ህብረት እንዲሁም ከኮሜሳ የተውጣጣው ልዑክ ከምርጫ እና የመልካም አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክሮችን አድርገዋል። በውይይቶቹ የዛምቢያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለምአቀፍ ትብብር ሚኒስቴር፣ የዛምቢያ ምርጫ ኮሚሽን፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች፣ የኮሜሳ ዋና ፀሐፊ፣ የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል። ምክክሩ በዋናነት በዛምቢያ ያለውን የቅድመ ምርጫ ድባብ እንዲሁም የምርጫ አስፈጻሚ ተቋማትን ዝግጁነት በመፈተሽ ላይ ያተኮረ ነው። በተጨማሪም ነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒ፣ ግልጽ እና አካታች እንዲሆን እየተከናወኑ ባሉ ጥረቶች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ማህበራዊ
ሀገራዊ ምክክሩ የትውልድን የተሻለ መፃኢ እጣ ፋንታ የሚወስን ወሳኝ መድረክ ነው
May 9, 2026 63
አዲስ አበባ ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የትውልድን የተሻለ መፃኢ እጣ ፋንታ የሚወስን ወሳኝ የጋራ መድረክ መሆኑ ተገለጸ። ወጣቶች በሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ ሀገራዊ መግባባትን በሚፈጥሩ የመፍትሔ ሃሳቦች ላይ ግንባር ቀደም ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባም መልዕክት አስተላልፈዋል። በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ የልዩነት ሃሳቦችን በምክክር በመፍታት በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ትውልድ ለመፍጠር ሀገራዊ ምክክር አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል። በሁሉም ክልሎች፣ በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ከሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችና አደረጃጀቶች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ በስኬት ተጠናቋል። በዚህም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ማጠናቀቁን ተከትሎ ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል። የክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ምክክሩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን በማስፈን ዘላቂ ሰላምና አንድነትን ለማምጣት ወሳኝ መድረክ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የፈጠረውን ዕድልም በታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና መሰል ጉዳዮች በሚስተዋሉ ዋና ዋና ሀገራዊ የሃሳብ ልዩነቶች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽነር ማርቆስ ማቲዎስ፤ ሀገራዊ ምክክር ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንቢያ መሳሪያ ነው ብለዋል። ወጣቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችም ሀገራዊ ምክክር የፈጠረውን ዕድል በመጠቀም የኢትዮጵያን መፃኢ እጣፋንታ የተሻለ ለማድረግ በትብብር መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሱልጣን አሊ፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የትውልድን መፃኢ እጣ ፋንታ የሚወስን ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል። በዚህም በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሂደት ወጣቶች ከፍተኛ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል። በቀጣይም ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሚካሄድበት ወቅት ወጣቶች ገንቢ ሚና እንዲወጡ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማኅበር አባል በቃሉ መሰረት፤ በክልሉ የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎች ላይ በንቃት መሳተፋቸውን አስታውሷል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርም በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጿል። በቀጣይም ዋናውን ሀገራዊ ምክክር በማካሄድ ሂደት ገንቢ ሚና እንደሚወጡ ተናግረዋል።
በዞኑ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ እየተከናወኑ ነው
May 9, 2026 75
ገንዳ ውኃ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦በምዕራብ ጎንደር ዞን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተከናወኑ መሆናቸውን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። አስተዳደሩ ፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ከተሰኘ አጋር አካል ከ27 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የትምህርት ቁሳቁስና የመማሪያ ክፍል ግንባታ ርክክብ ዛሬ በገንዳ ውሃ ከተማ አካሄዷል።   የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንዳሉት፤ በዞኑ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻልና የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅ ቁልፍ ተግባር ሆኖ እየተከናወነ ይገኛል። በትምህርት ዘርፉ የሚደረጉ ድጋፎች የነገውን ትውልድ ግንባታ ታሳቢ ያደረገ እገዛ በመሆኑ የሚደነቅና ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር ነው ብለዋል። የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ አያና በበኩላቸው፤ የትምህርት ተቋማትን ተደራሽነት በማሳደግና አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   የመማር ማስተማር ስራውን የተሳለጠ በማድረግ በኩል ባለፉት ጊዜያት በትብብር የተሰሩ ስራዎች ውጤት የታየባቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ዛሬ የተደረገው ድጋፍ የነበረውን ችግር የሚፈታ መሆኑን ተናግረዋል። ለመማር ማስተማር ስራው ውጤታማነት እየተደረጉ ያሉ የድጋፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያረጋገጡት ደግሞ በፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የመተማ ጽህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ ማርቆስ ሞላ ናቸው።   ድጋፉም ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር፣ የፈተና ወረቀት ማባዣ ሪዞ ማሽን፣ አዲስ የተገነቡ አራት የመማሪያ ክፍሎችና ሙሉ ጥገና የተደረገላቸው ሁለት ብሎኮችን ያካተተ ነው። በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የዞኑ አመራሮች፣ የድርጅቱ ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በጉራጌ ዞን የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይጠናከራሉ
May 9, 2026 60
ወልቂጤ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ተናገሩ። በወልቂጤ ከተማ በጉብሬ ክፍለ ከተማ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይም አቶ ላጫ ጋሩማ እንደተናገሩት፤ ፕሮጀክቶቹ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማዕከል ያደረጉ ናቸው።   ከፕሮጀክቶቹ የማህበረሰብ መድኃኒት ቤት ግንባታ፣ የፍርድ ቤት ህንፃ እና የህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ግንባታዎች ተጠቃሽ እንደሆኑ ገልጸው ህብረተሰቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ያስችላሉ ብለዋል። በመሆኑም መሰል የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር በበኩላቸው፤ በከተማው የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመንደፍ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።   በተለይም የህዝብን ጥያቄ የሚመልሱ እና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ መሆኑን አክለዋል። በወልቂጤ ከተማ የጉብሬ ክፍለ ከተማ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበሩት እነዚህ ፕሮጀክቶች ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸው መመረቃቸውን ተናግረዋል። የተገነባው የማህበረሰብ አቀፍ መድኃኒት ቤትም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትንና ጥራትን ለማረጋገጥ እንደሚያስችልም አመልክተዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ወርቅነሽ ወልዴ፤''በከተማችን በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራቱ የተረጋገጠ መድኃኒት እንድናገኝ መደረጉ ለህብረተሰቡ ጤና ትኩረት መሰጠቱን የሚያሳይ ነው'' ብለዋል፡፡   ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ዚያድ በደዊ ከግል መድኃኒት ቤቶች በከፍተኛ ዋጋ መድሃኒት ይገዙ እንደነበር ጠቅሰው በቅርበት በማግኘታቸው መደሰታቸውን ጠቅሰዋል።   በቅርበት የክልሉ ምድብ ችሎት ተከፍቶ መስራቱ ችግራቸውን እንደሚያቀልላቸው የተናገሩት ደግሞ አቶ አብዲ አሺቅ ናቸው። ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁ መሰረተ ልማቶች የተሻለ ጥቅም እንዲሰጡ አስፈላጊውን ጥበቃና እንክብካቤ እንደሚያደርጉም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
ኢኮኖሚ
የመረጃ ስርዓቱ ሳይንሳዊ መንገዶችን በመከተል አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው
May 9, 2026 25
ሰመራ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ብሔራዊ የግጦሽ መሬት የጤና ክትትል የመረጃ ስርዓት ሳይንሳዊ መንገዶችን በመከተል አርብቶ አደሩን እና ከፊል አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገለጸ። በአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች ተግባራዊ የሚደረግ ብሔራዊ የግጦሽ መሬት የጤና ክትትል የመረጃ ስርዓት ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ዛሬ በሰመራ ተካሄዷል። በመድረኩም ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ዑመር ኑሩ እንደገለፁት፤ በክልሉ የአርብቶ አደሩንና ከፊል አርብቶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባራት ይጠናከራሉ።   የአርብቶ አደሩ ህይወት ከእንስሳት ሀብቱና ከግጦሽ መሬቱ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ መሆኑን አውስተው የመረጃ ስርዓቱ ሳይንሳዊ መንገዶችን በመከተል አርብቶ አደሩን እና ከፊል አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ እንደሚያደርገው ገልጸዋል። የመረጃ ስርዓቱ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በመሬት መራቆትና በመጤ አረሞች ምክንያት ጉዳት ለደረሰበት መሬት መፍትሄን ይዞ የመጣ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑንም አክለዋል። በተለይም የአዋሽ ወንዝን ተከትሎ በርካታ አካባቢዎች በመጤ አረም በመወረራቸው ሳቢያ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን ጠቁመው ችግሩን ለመቅረፍም ሳይንሳዊ ዘዴን በመጠቀም ጥረት መደረጉ የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ያሳድገዋል ብለዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የእንስሳትና ንግድ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዮሴፍ መካሻ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመረጃ ስርዓቱ በተለይም ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ነው ብለዋል።   በተጨማሪም ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለትምህርት ተቋማትና ሌሎች አካላት መረጃ በመስጠት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ እገዛ እንደሚያደርግም አክለዋል። ስርዓቱ ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ለግጦሽ የሚውሉ ስፍራዎችን በመለየት፣ የተራቆቱና ጉዳት የደረሰባቸው እንዲታወቁ አስፈላጊውን መረጃ በማድረስ ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም መሐመድ ናቸው።   ይህም በክልሉ ያለውን የዘርፉን አቅምና ክፍተት በመለየት ለምርታማነት መጨመር ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም አክለዋል።
የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በተግባር የሚለካ ውጤት የተገኘባቸው ናቸው
May 9, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በተግባር የሚለካ ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በስድስት ክፍለ ከተሞች ግንባታቸው የተጠናቀቁ የብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሕንፃዎችን መርቀዋል።   በዚሁ ወቅት እንዳሉትም፤ ግንባታቸው ተጠናቆ የተመረቁ የብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሕንፃዎች የጋራ ትርክት በማስረፅ ሕብረብሔራዊ አንድነት የሚጠናከርባቸው ናቸው። የኢትዮጵያ ብልፅግና በማረጋገጥ የሀገረ መንግስት ግንባታ የሚጠናከርባቸውና ጀምሮ የማጠናቀቅ ልምምድ ዕድገት ወሳኝ ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ዓመታት ፈተናን ወደ ድል በመቀየር በሁሉም መስክ አመርቂ የልማት ውጤቶች የተመዘገቡባቸው መሆናቸውን ተናግረዋል። አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ በተያዘው ግብ መሠረትም በመዲናዋ በሁሉም መስክ ስምና ገፅታዋን የሚመጥን የልማት ሥራ መሰራቱን አንስተዋል። የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶችም የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በተግባር የሚለካ አመርቂ ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን አስረድተዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን ህብረብሄራዊ አንድነትና የጋራ ትርክት በማጠናከር ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በትጋት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
የደሴ ከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት መምሪያ ውጤታማ ለሆኑ ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግርና የእውቅና ስነ-ስርዓት
May 9, 2026 63
ደሴ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ የደሴ ከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት መምሪያ ውጤታማ ለሆኑ ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግርና የእውቅና ስነ-ስርዓት ማካሄዱን አስታወቀ። በመድረኩ ላይ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ እንደገለፁት፤ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር የከተማዋን ሰላም በማስጠበቅና ልማትን በማፋጠን ረገድ በትኩረት ተሰርቷል። ይህም የከተማዋን ፀጋ በማልማት ለዜጎች የስራ እድል ከመፍጠር ባሻገር ውጤታማ እንዲሆኑ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል። በተደረገው ድጋፍም ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር በማድረግ ወደ በላቀ ሁኔታ ተግባራቸውን ለመወጣት እንዲችሉ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱልሃሚድ ይመር በበኩላቸው፣ በዛሬው እለትም ስምንት ኢንተርፕራይዞች ወደ ባለሃብትነት እንዲሸጋገሩ መደረጉን አስረድተዋል። በተጨማሪም 20 ኢንተርፕራይዞች ባሳዩት የተሻለ የስራ አፈጻጸም እውቅና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመው ይህም በቀጣይ ውጤታማነታቸውን በማስቀጠል ወደ ባለሃብትነት ለማሸጋገር ያለመ ነው ብለዋል። ኢንተርፕራይዞቹም ወደ ባለሃብትነት የተሸጋገሩት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብርና ከዚያ በላይ ካፒታል በማስመዝገባቸውና በስራቸው በቀጠሩት የሰው ሃይል ተመዝነው መሆኑን አመልክተዋል። የደረጃ ሽግግር ላደረጉ ኢንተርፕይዞች የቦታና የብድር አቅርቦት በማድረግ ፈጥነው ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግም አስረድተዋል። መቅደስና ጓደኞቿ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች ማህበር አስተባባሪ መቅደስ መሰለ እንደገለጸችው፣ በ10 ሺህ ብር ካፒታል የጀመረችው ስራ አሁን ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማድረስ መቻሏን አስረድታለች። ካፒታሏን ማሳደግ የቻለችውም የተለያዩ ቦርሳዎችን፣ ቀበቶዎችንና ሌሎች የቆዳ ምርቶችን በማምረትና በመሸጥ መሆኑን ጠቁማ ከ20 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሏን ገልጻለች። በብረታ ብረት ስራ ላይ የተሰማራው ወጣት አብዱራህማን እንድሪስ በሰጠው አስተያየት በተሰማራበት ዘርፍ ፋብሪካዎችና ማሽኖች ግብዓት በማምረት ለውጤት መብቃቱን ተናግሯል። በከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ23 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።  
በክልሉ በአንድ ወር ውስጥ ከ17 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተሻሻለ የቡና ችግኝ ተሸፍኗል
May 9, 2026 77
ዲላ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባለፈው አንድ ወር ከ17 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተሻሻለ የቡና ችግኝ መሸፈኑን የክልሉ ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል ብሩ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ለቡና ልማት ተስማሚ የሆነውን ስነ ምህዳር በመጠቀም የቡና ማሳን የማስፋፋት ሥራ እየተከናወነ ነው።   በተያዘውም ዓመት ከ19 ሺህ ሄክታር በላይ አዲስና ያረጀ ቡና እድሳት በሚከናወንበት መሬት ላይ በበልግ እና በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በተሻሻለ የቡና ዝርያ ለመሸፈን ወደተግባር ተገብቷል። በዚህም ካለፈው የሚያዚያ ወር ጀምሮ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከ40 ሚሊዮን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ተከላ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። ባለፈው አንድ ወርም ከ17ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተሻሻለ የቡና ችግኝ ተሸፍኗል ያሉት አቶ አማኑኤል፣ ከዚህ ውስጥ ከ5 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም የለማ እንደሆነና ይህም በክልሉ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ይህም የክልሉን በሄክታር 10 ኩንታል አማካይ የቡና ምርታማነት በቀጣይ ዓመታት ወደ 12 ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ አስረድተዋል። በዞኑ ያረጀ ቡና በማንሳት በተሻሻሉ ዝርያዎች በኩታ ገጠም የመተካቱ ተግባር ውጤት ማምጣቱን ያነሱት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተገኝ ታደሰ ናቸው።   እሳቸው እንዳሉት በዞኑ ባለፈው ሚያዚያ ወር ብቻ ከ5 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ 11 ሚሊዮን የቡና ችግኞች ተከላ ተከናውኗል። ከዚህ ውስጥ 1 ሺህ 200 ሄክታር መሬቱ በተደራጁ አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም እንዲለማ የተደረገ ነው።   ‎‎በዞኑ ዲላ ዙሪያ ወረዳ የሽገዶ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ያቆብ ማሮ በበኩላቸው፤ በማሳቸው የነበረው ቡና በእርጅና ምክንያት ምርት ወደማይሰጥበት ደረጃ ደርሶ እንደነበር ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት እሳቸውን ጨምሮ 75 የአካባቢው አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም ተደራጅተው በ46 ሄክታር መሬት ላይ ያረጀ ቡና አንስተው በተሻሻለ የቡና ዝርያ መተካታቸውን ተናግረዋል።  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በጅማ ዩኒቨርሲቲ የበለፀገው "ሀቂላ ላብ" የተሰኘው መተግበሪያ ቀልጣፋ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ እያደረገ ነው
May 9, 2026 89
ጅማ ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦በጅማ ዩኒቨርሲቲ የበለፀገው "ሀቂላ ላብ" የተሰኘውና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የታገዘው መተግበሪያ ቀልጣፋ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ። ዩኒቨርሲቲው የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ "2030" ግቦችን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ውስጥ መምህራንና ተማሪዎችን ያሳተፉ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎችን እያበረከተ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል በ "ሀቂላ ላብ" ፕሮጀክት ስር የበለጸገውና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የታገዘው የጤና መተግበሪያ አንዱ ሲሆን ''ሀቂላ'' የአፋን ኦሮሞ ቃል ሲሆን ጥበብ የሚል ትርጓሜን እንደያዘም ተገልጿል። በዚሁ ስያሜ የሚታወቀው መተግበሪያ በ2014 ዓ/ም የፖሊዮ በሽታን ለመለየት በሚል ታስቦ የተሰራና አሁን ላይ ግን አምስት ዓይነት በሽታዎችን እንዲለይ ተደርጎ ወደ ትግበራ ገብቷል። መተግበሪያው በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ቋንቋዎቹን ወደ አምስት የማሳደግ ውጥን እንዳለም ተመልክቷል። በወቅቱ መተግበሪያው የፅሁፍ መረጃን ብቻ ወስዶ የበሽታውነ ዓይነት እንዲለይ የተሰራ ቢሆንም ኋላ ላይ በተደረገለት ማሻሻያ የፎቶ እና የተንቀሳቃሽ ምስል መረጃን በመጠቀም አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል። የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ትብብር ምክትል ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ሙሉእመቤት አበራ እንደገለፁት፤ ተቋሙ ባለፉት ሶስት ዓመታት ብቻ በግብርና፣ በጤና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ከ 140 በላይ ማህበረሰብ ተኮር ምርምሮችን አከናውኗል። ይህም የማህበረሰቡን ችግር ከመፍታት ባሻገር የዕውቀት ሽግግር እንዲሳለጥ የበኩሉን ሚና መወጣቱን ተናግረዋል። በዚህም በ "ሀቂላ ላብ" ፕሮጀክት ስር የበለጸገውና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የታገዘው የጤና መተግበሪያም በመምህራን እና ተማሪዎች ተሳትፎ እውን ሊሆን መቻሉን አመልክተዋል። የፕሮጀክቱ ዳይሬክተር ገላን አያና (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ መተግበሪያው መጀመሪያ ላይ የፖሊዮ በሽታን ለመለየት ታስቦ የተሰራ መሆኑን ጠቁመው አሁን ላይ ወባንና ኩፍኝን ጨምሮ አምስት ዓይነት በሽታዎችን የመለየት አቅም እንዲኖረው ተደርጓል ብለዋል።   በአሁኑ ወቅት መተግበሪያው በጅማ ከተማ እና በሰቃ ወረዳ በሚገኙ 8 የጤና ተቋማት፣ በሸነን ጊቤ ሆስፒታል እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የህክምና ማዕከል አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።   በሸነን ጊቤ ሆስፒታል የጤና ባለሙያ የሆኑት ወይዘሮ ሀሊማ አባተማም፣ መተግበሪያው ስራቸውን በእጅጉ እንዳቀለለላቸው ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም በሽታዎችን ለመለየት ከ30 እስከ 40 ደቂቃዎች ይወስድ እንደነበር ገልጸው የ "ሀቂላ" መተግበሪያን በመጠቀም ወደ10 ደቂቃ ዝቅ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። አገልግሎቱን ከጅማና አካባቢዋ በተጨማሪ ወደ ሌሎች ዞኖች ለማስፋፋት የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑም ተመላክቷል።
በዩኒቨርሲቲው የሚሰሩ የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግር ለማቃለል እና ሀገራዊ እድገትን የሚያፋጥኑ ናቸው
May 9, 2026 84
ደብረ ብርሃን፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሚያወጣቸው የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግር ከማቃለል ባለፈ ሀገራዊ እድገትን ለማፋጠን የሚያግዙ መሆናቸውን አስታወቀ። የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 5ኛውን ዓለም ዓቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ እያካሔደ ነው። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለሰ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ዘርፉን በማጠናከር የአካባቢውን ማህበረሰብ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በቴክኖሎጂና መሰል ዘርፎች ተግባር ተኮር የምርምር ስራዎችን እያካሄደ መሆኑን ነው የተናገሩት። የምርምር ስራዎቹ የማህበረሰቡን ችግር ከማቃለል ባለፈ ሀገራዊ እድገትን በሚያፋጥን አግባብ እንዲተገበሩ አቅዶ እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። የዩኒቨርስቲው ጥናትና ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ሲሳይ ሙላት (ዶ/ር) በበኩለቸው፤ ዩኒቨርሲቲው ከሀገር ውስጥና ከውጭ የምርምር ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሀገር በቀል እውቀቶቸን ጥቅም ላይ ለማዋል የጀመራቸው ተግባራት ተስፋ ሰጪ ናቸው ብለዋል። በኮንፍረንሱ 27 የምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን ተግባራዊ እንዲሆኑም በቅንጅት እንደሚሰራም ነው ያመለከቱት። በኮንፍረንሱ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት የማታው አዲስ (ዶ/ር)፤ ለጤናና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውል አዲስ ቴክኖሎጂ ላይ ያደረጉትን የምርምር ስራ አቅርበዋል። የምርምር ኮንፍረንሶች እርስ በእርስ ትስስር በመፍጠር የምርምር ስራዎችን በቅንጅት ወደ ተግባር ለማሸጋገር እንደሚያግዙም አመልክተዋል። ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ኢርፖሴ ኢንስኔ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የምርምር ኮንፍረንሶች የጋራ ሃሳብን በማፍለቅ የሀገርን ኢኮኖሚና ማህበራዊ አቅም ለማሳደግ ያግዛሉ ብለዋል።
በኢትዮጵያ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ህግ መኖር ለሀገራዊ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ መሰረት ነው
May 8, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ህግ መኖር የሀገርን ቁልፍ መሰረተ ልማቶች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ መሰረት መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ። ቋሚ ኮሚቴው የቁልፍ መሰረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።   ምክትል ሰብሳቢው ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የረቂቅ አዋጁ መዘጋጀት መሰረተ ልማቶችን ከጥቃት በመከላከል ረገድ ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት እንዳይጎዳ ለማድረግ ያስችላል። ረቂቅ አዋጁ ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ለይቶ ያካተተ መሆኑን አንስተው፤ ተቋማቱ ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ በመሆናቸው ለሳይበር ጥቃት እንዳይጋለጡ በማድረግ ረገድ አዋጁ ትልቅ ውጤት እንደሚያመጣ ተናግረዋል። ሰብሳቢው አክለውም፣ አዋጁ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል ወሳኝ ሚና እንደሚኖረውና ብሄራዊ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ጠንካራ የህግ ማዕቀፍ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው፤ ተቋሙ የሀገሪቷን መሰረተ ልማቶች ከመጠበቅ አኳያ በርካታ ፖሊሲዎችን፣ አዋጆችንና ደንቦችን እየተገበረ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።   ይህ ረቂቅ አዋጅ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልጸው፣ በጋራ መስራት በዘርፉ ውጤታማነትን እንደሚያረጋግጥ አመልክተዋል። ዲጂታል ኢኮኖሚን በስፋት መጠቀም በሚገባን ልክ ሊከተሉ የሚችሉ ስጋቶችን ለመከላከልና ተገቢውን ጥበቃ ለማድረግ እንዲሁም ለቁልፍ ተቋማት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ አዋጁ ትልቅ ዕድል ይዞ እንደሚመጣም አስገንዝበዋል። በመድረኩ የተገኙ ባለድርሻ አካላት ረቂቅ አዋጁ የሀገሪቷን ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ለተግባራዊነቱ በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በተጨማሪም በዘርፉ በቂና ብቁ ባለሙያዎችን የማፍራት እንዲሁም መንግስት ከግሉ ዘርፍ ጋር በጋራ የመስራት አስፈላጊነት ላይ አስተያየታቸውንና ማብራሪያ የሚሹ ነጥቦችን አቅርበዋል። ዋና ዳይሬክተሯ ትዕግስት ሀሚድ ለተነሱት ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፤ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ለሳይበር ደህንነት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ በቀጣይ በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በዘርፉ በቂ የሰው ኃይል እየፈራ መሆኑን አንስተው፣ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) በማጠቃለያቸው፤ አስተማማኝ የሳይበር ደህንነትን በኢትዮጵያ ለማረጋገጥ ከመድረኩ የተገኙ ጠቃሚ ግብዓቶችን በመጠቀም አዋጁን ለተግባራዊነት ለማዘጋጀት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
የአፍሪካን እውነት ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል
May 8, 2026 161
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን እውነት ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች ገለጹ። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛል። ጉባኤውም ኃላፊነት የሚሰማቸው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማጠናከር፣ ትብብርን ለመፍጠርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ግብን ለማሳካት ያለመ ነው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣የአህጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶችን ለማስመዝገብና የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር የጋራ ምክክር ያደርጋሉ።   በጉባኤው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፣ የኤ.ጂ.ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገመዳ ኦላና፣ የአፍሪካ ህብረት ተወካዮችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። በጉባኤው ላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ዝግጅቶች ላይ ያለውን አስተዋጽኦ የሚዳስስ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የናቹራል ላንጉዌጅ ፕሮሰሲንግ ምርምር ዲቪዥን ዳይሬክተር ሳሙኤል ራህመቶ፤ ቀደም ሲል የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለባለሙያዎች የቴክኒክና የምርምር ሥራ ይውል እንደነበር ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ የማህበረሰቡን የዕለት ተእለት የሥራ እንቅስቃሴ ቀለል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣን ዕድገትም ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ የፕሮዳክሽን ሥራዎችን የሚያከናውን ምኅዳር በመፍጠር እንደ ሲኒማ የሚታዩ ምስሎችን መፍጠር እያስቻለ መሆኑን አንስተዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምስልና ድምፅ የማመንጨት አቅም ዕድገት የይዘት ፈጣሪዎችን ሥራ እያገዘ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለይዘት ዝግጅት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለአህጉሪቱ ትርክትና ገፅታ ግንባታ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።   የአህጉሪቱን እውነተኛ ባህልና ታሪክ ለዓለም ማህበረሰብ ለመተረክም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። ሌላኛው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ብራያን ጆታ በበኩሉ፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጠራን በማላቅ የዲጂታል ክህሎትን የሚያበለፅግ የቴክኖሎጂ አማራጭ መሆኑን ገልጿል። በዚህም የአፍሪካን እውነተኛ ገፅታ ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የዲጂታል አማራጭ ክህሎትን በማሳደግ መጠቀም እንደሚያስፈልግ ተናግሯል። ቦትስዋናዊው ታዋቂ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪ ዊሊያምላስት ኬ.አር.ኤም፤ የይዘት ፈጠራ ሥራዎችን ከገንዘብ ማግኛና ቁጥር ባሻገር ለአህጉሪቱ ትርክት ግንባታ መጠቀም አለብን ብሏል። ለዚህም የሥራ ፍቅር ባህልን በማዳበር የዲጂታል አማራጮችን የአፍሪካን የተሻለ ገፅታና ትርክት በሚያጎላ መልኩ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጿል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 31ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል
May 9, 2026 94
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከመቻል በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ ቡና በ42 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቻል በ48 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡናማዎቹ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አላሸነፉም። በ30ኛ ሳምንት መቻል ከአዳማ ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ሁለቱም ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። መቻል ካሸነፈ ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ዝቅ ያደርጋል። በሌላኛው መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመቀሌ 70 እንደርታ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ36 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በ30 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች፣ መቀሌ 70 እንደርታ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም። ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ እና መቀሌ 70 እንደርታ ደግሞ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ ለማግኘት የሚያደርጉት ነው። ሀዲያ ሆሳዕና ከሃዋሳ ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ባለፉት አራት ጨዋታዎች ከድል የራቀው ሀዲያ ሆሳዕና በ35 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሃዋሳ ከተማ በ44 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሰባት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ሁለቱም ቡድኖች የአሸናፊነትን መንገድ ለማግኘት ይጫወታሉ። ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከምድረ ገነት ሽሬ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። አዳማ ከተማ በ35 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ምድረ ገነት ሽሬ በ33 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ባለፉት 10 የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው አዳማ ከተማ ሶስት ነጥብ ለማግኘት እና ከወራጅ ቀጠና ስፍራ ለመራቅ ይጫወታል። በ30ኛ ሳምንት ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 ያሸነፈው ምድረ ገነት ሽሬ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ወደ ሜዳ ይገባል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 31ኛ ሳምንት እስከ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ሲዳማ ቡና በ55 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በ14 ጎሎች ይመራል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋቾች የሆኑት አዲስ ግደይ እና ናትናኤል ዳንኤል በተመሳሳይ 10 ግቦች ይከተላሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ ስኬታማ የልማት መርሃ ግብሮች የበለፀገ የደን ሃብት እንዲፈጠር እያደረገ ነው
May 9, 2026 74
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ ስኬታማ የልማት መርሃ ግብሮች የበለፀገ የደን ሃብት እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በተያዘው በጀት ዓመት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት መርሃ ግብር 3 ነጥብ 9 ሚሊየን ሄክታር መሬት መልማቱንም አስታውቋል። በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈፃሚ ፋኖሴ መኮንን፤ የሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋ የፈጠረው የደን መመናመን ከፍተኛ የአካባቢ መራቆትን አስከትሎ ነበር ብለዋል። ይህም የኢትዮጵያ የአፈር ለምነትን በመቀነስ በግብርና ምርታማነት፣ በዱር እንስሳትና ዕፅዋት ደኅንነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል። በዚህም በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ማግስት በአረንጓዴ አሻራና የአካባቢ ጥበቃ ልማት መርሃ ግብር የሥነ-ምኅዳር ደኅንነት እንዲያገግም ያስቻለ ስኬታማ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በተለይም በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ የህብረተሰቡን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትን ባህል በማጎልበት የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን እያስጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመትም በ22ሺህ 59 ተፋሰሶች 4 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለማልማት በተያዘው ዕቅድ፤ እስካሁን 3 ነጥብ 9 ሚሊየን ሄክታር መሬት በበጋ ተፋሰስ መልማቱን አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅትም በተለያዩ ክልሎች የሥነ-ምኅዳር ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ የልማት ሥራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት ዓመታት በህብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ሰፋፊ የአፈርና ውሃ ጥበቃ የልማት ሥራዎችም የተራቆተ የመሬት ገፅታ እንዲያገግም በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን አስረድተዋል። የህብረተሰቡ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ባህል እያደገ መምጣቱም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም በርካታ ዜጎች በንብ ማነብ፣ እንስሳት መኖ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት መርሃ ግብሮች ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። ይህም የህብረተሰቡን የአካባቢ ጥበቃ ባለቤትነትን በማረጋገጥ ኢትዮጵያ በደን ሀብት የበለጸገች ለምለም ሀገር እንድትሆን እያደረጋት መሆኑን አንስተዋል።  
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል
May 9, 2026 79
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡ ተገለጸ። በቢሮው የደን ልማት እንክብካቤ ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን ስዩም ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክረምቱ ወቅት ለሚከሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር የደን ሽፋንን በመጨመር፣ የደረቁ ምንጮች እንዲያገግሙ በማድረግ እና የግጦሽ መሬት መጠንን በመጨመር አመርቂ ውጤት ተመዝግቦበታል ነው ያሉት፡፡   በአሁኑ ወቅትም በክልሉ 71 ተራሮችን የማልማት ስራ እየተከናወነ ሲሆን ቡለውጡ አመታት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት 18 ነጥብ 9 ከመቶ የነበረውን የደን ሽፋን ከ 23 ነጥብ 8 በመቶ በላይ ማድረስ መቻሉንም ተናግረዋል። ይህንን ለማስቀጠልም በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 180 ሺህ ሔክታር መሬት በተለያዩ ችግኞች ለመሸፈን እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት ። ለዚህም የችግኝ፣ የጉድጓድ እና ሌሎች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች በበቂ ሁኔታ መደረጉን አመልከተው በአሁኑ ወቅትም የበልግ ወቅት የችግኝ ተከላ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። የችግኝ ተከላው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ትልቅ አበርክቶ እንዳለው አመልክተው ለክረምት ወቅት ተከላ የሚደረገው ዝግጅት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በዘርፉ የተመዘገበውን ለውጥ ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ሊረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዞኑ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል
May 8, 2026 186
ጊምቢ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ በምእራብ ወለጋ ዞን ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታቸው የጎላ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ እንዳሉት በዞኑ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል። ከችግኞቹም መካከል ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታቸው የጎሉ የቡና፣ የአቮካዶ፣ የማንጎ፣ የፓፓያ እና ሌሎች እንደሚገኙበት አስረድተዋል። የችግኝ ተከላው በበጋ ወራት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ፣ ለእንስሳት መኖ እንዲውልና ለም አፈር በጎርፍ እንዳይወሰድ ለመከላከል ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱ ተገልጿል።   ይህም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ችግኞቹን በበጋ ወራት በተከናወኑ የተለያዩ የእርከን ስፍራዎችና የተመረጡ ቦታዎች ለመትከልም እስካሁን ከ117 ሚሊዮን በላይ ጉድ ጓዶች ቁፋሮ መከናወኑን አቶ ፍቅሩ ጠቅሰዋል። ስራውን ለማሳካትም አርሶ አደሩን በማሳተፍ መከናወኑን የጠቀሱት ሀላፊው፤ የግብርና ባለሙያች ድጋፍና ክትትል ስራዎች መጠናከራችውን አንስተዋል። ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውን የጠቀሱት ደግሞ የጊምቢ ወረዳ አርሶ አደር ዋኬኔ አምሳሉ ናቸው። ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞችን ጽድቀት መጠን ለማሳደግ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በመንከባከብ ከሰውና እንስሳት ንክኪ መጠበቃቸውን ተናግረዋል። ዘንድሮም በመንግስት ከሚለሙት ችግኞች ባለፈ እሳቸው በግላቸው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞችን ማፍላታቸውን ጠቁመዋል። ከዚህ በፊት ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት ባለመስጠታቸው ያጡትን ምርታማነት በሚያካክስ መልኩ በመጪዉ ክረምት የሚተከሉ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች በብዛት ማዘጋጀታቸው የገለጹት የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ለሊሳ ኤቢሳ ናቸው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በተሰራው ስራ በርካታ ጥቅም በማግኘታቸውም ስራውን ለማስቀጠል ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ልማት ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ አድርጓል
May 8, 2026 187
ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች የክልሉን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረጋቸውን የክልሉ አካባቢና ደን ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢኒሼቲቭ የተራቆቱ አካባቢዎችን አረንጓዴ በማልበስና የአካባቢን ሥነ ምህዳር በማስተካከል አርሶ አደሩን ተጠቃሚ እያደረገ ነው።   የአማራ ክልል አካባቢና ደን ጥበቃ ባለስልጣን ሃላፊ ተስፋሁን አለምነህ ለኢዜአ እንደገለጹት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በክልሉ ከተጀመረ ወዲህ በክልሉ የደን ሽፋን ላይ አበረታች ለውጥ ታይቷል። ለዚህም ባለፉት ዓመታት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች የክልሉን የደን ሽፋን ቀደም ሲል ከነበረበት 13 ነጥብ 8 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ማሳደጋቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።   ልማቱ የተራቆቱ አካባቢዎች በአረንጓዴ እንዲሸፈኑ፣ የአፈር መሸርሸር እንዲቀርና ለምነቱ እንዲጨምር እንዲሁም የከርሰና የገጸ ምድር ውሃ እንዲጨምር አስችሏል ብለዋል። በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በለሙ አካባቢዎች አርሶ አደሩ የእንስሳት መኖን ጨምሮ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ቸግኞችን በመትከል ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱንም አመልክተዋል። በተለይ መርሀ ግብሩ በእንስሳት እርባታ፣ በእንስሳት ማድለብ፣ በወተት ልማትና በንብ ማነብ ሥራ ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ነው ያስታወቁት።   በክልሉ ግብርና ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር እስመለዓለም ምህረት በበኩላቸው፣ በዘንድሮ ክረምትም የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል አረንጓዴ አሻራን አጠናከሮ ለማስቀጠል ዝግጅት እየተደረገ ነው። እስካሁንም ዘንድሮ ከሚተከለው አጠቃላይ ችግኝ 94 በመቶ የሚሆነው ተፈልቶ ለተከላ መዘጋጀቱን ጠቁመው፣ ለችግኝ ተከላም ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ተዘጋጅቷል ብለዋል። በአማራ ክልል ባለፈው የክረምት ወቅት ከተተከሉ አጠቃላይ ችግኞች ውስጥ 86 በመቶ የሚሆኑት መጽደቃቸውን በመጀመሪያ ዙር በተካሄደ ቆጠራ መረጋገጡን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት ይገባል 
Apr 28, 2026 1034
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት እንደሚገባ የሕብረቱ ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃጸም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 ጎን ለጎን የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው።   የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድን ሀገር በቀል በማድረግ አካታች ዕድገትና ዘላቂ የኢኮኖሚ ሽግግርን የሚያፋጥን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ገልጸዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራትም ብሔራዊ የልማት ዕቅዶችን ከአጀንዳው ጋር በማጣጣም የበጀት ድልድልና የፖሊሲ እርምጃዎችን ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካ አጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦች የበለጸገች አህጉርን እውን ለማድረግም የአባል ሀገራት ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። የአጀንዳ 2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን በማሳካት የተሳለጠ የለውጥ ሽግግርን ለመፍጠርም ጠንካራና የተሰናሰለ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና አህጉራዊ የፖሊሲ ፍሰት ሊኖር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ለዚህም የመንግሥታት፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች በወሳኝ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ የሚኖራቸውን ትብብርና ቅንጅት የሚያበረታታ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።   የዑጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትርና ተሰናባቿ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ ቢሮ ሊቀ-መንበር ሮቢናህ ናባንጃ በበኩላቸው፤ የአፍሪካውያን ድምፅ በወሳኝ የዓለም መድረኮች ላይ መንፀባረቅ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ መድረኮች በከፍተኛ ደረጃ ከሚደረግ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ባለፈ በወሳኝ ስትራቴጂክ ሂደቶች ላይ በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ብለዋል። የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካትም ሎጂስቲክስ፣ ትራንስፖርትና መሰል የትኩረት ዘርፎች ላይ በስፋት በመሰማራት ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች ነው
Apr 28, 2026 574
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃፀም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 በትይዩ የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው። በአፍሪካ አካታች ዕድገትና ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ሽግግር ለመፍጠር ወሳኝ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድ ሀገር በቀል እንዲሆን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ተናግረዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራት ብሔራዊ የልማት ዕቅዶቻቸው ከአጀንዳው ጋር እየተጣጣመ መምጣቱን በማንሳት፤ የበጀት ድልድልና ፖሊሲዎቻቸው ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ የሰጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን በማሳካት የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ በሀገራት መካከል ያለው ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባም አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸውን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ አለባቸው
Apr 27, 2026 580
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦‎ አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸው ላይ እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከታንዛኒያ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የአፍሪካ ወሳኝ ማዕድናትን ለአረንጓዴ የኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ማዋል" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጁት የ12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ቅድመ ጉባኤ ተካሂዷል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ እንደ ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ግራናይት እና ሌሎች የከርሰ ምድር ሀብቶችን ጨምሮ የዓለምን 30 በመቶ ማዕድናትን ይዛለች፡፡ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻዋን የዓለምን ከፍተኛ የኮባልት ማዕድን የያዘች መሆኑን ገልጸው፤ ይሄውም አፍሪካን የዓለም አቀፍ የኃይል ሽግግር /Energy Transition/ ማዕከል ያደርጋታል ብለዋል፡፡ አፍሪካ ዩራኒዬምና ሌሎች የከርሰ ምድር የከበሩ ማዕድናት ባለቤት መሆኗን በመጥቀስ፤ ለዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል አቅርቦት አስተዋጽኦ ከማድረግ ባለፈ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ኒውክሌር ኃይል ልማት እያመሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አፍሪካ የከበሩ ማዕድናት ባለቤት ብትሆንም አብዛኛው በጥሬ እቃ መልክ ወደ ውጭ የሚላክ በመሆኑ የአህጉሪቱ የእርስ በእርስ ግብይት ከሁለት በመቶ እንዳማይዘል ተናግረዋል፡፡ በአህጉሪቱ የማዕድናት ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን መገንባት ቢቻል በየዓመቱ ከ24 ቢሊየን ዶላር በላይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘትና ለ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ይቻላል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ የማዕድን ፖሊሲ ለእሴት መጨመር፣ ኢንዱስትሪ ልማትና ሁሉን አቀፍ ልማት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአህጉሪቱ የተቀናጀ ቀጣናዊ ኢንዱስትሪ ለመገንባት ያለውን ፍላጎት በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አህጉራዊ የማዕድን ሀብቶችን ወደ ዘላቂ ብልጽግና መለወጥ ይገባል ብለዋል፡፡ በዚህም የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቀጣናዊ እሴት ሰንሰለትን በማጠናከር የማዕድን ጸጋዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚደረገው ጥረት ትብብሩን ማጠናከሩን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካዳሪ ሲንጎ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍና አካታች ዕድገት ለማስመዝገብ የማዕድን ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በተፈጥሮ ሀብታችን ላይ የሚኖረን ትብብርና ተሳትፎ ስትራቴጂያዊና መዳረሻ ግብ ያለው መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮት ሽግግርን ለመፈጠር በአቅም ግንባታ ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 966
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ሐተታዎች
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ  ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 332
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች
May 3, 2026 448
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር እያሸጋገራት ይገኛል።የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የመሰረተ ልማት እና የተቋማት ግንባታ ስራዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋንኛ ስራዎች ናቸው። ለውጡን ተከትሎ መንግስት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን ስትራቴጂ በመቅረጽ የዲጂታላይዜሽን ስራውን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶ አድርጎታል። የለውጡ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ ቴክኖሎጂን እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመቁጠር "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን አጠቃላይ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ተግባር ገባ።ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱን የዲጂታል ጉዞ ከመሰረቱ የለወጠ ሲሆን፣የመጀመሪያው ትልቅ እርምጃም የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ነበር። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ የኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል።በተለይም የአምስተኛ ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን አስችሏታል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ለውጡ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ውጤት አምጥቷል።እንደ ቴሌብር (telebirr) ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ምንም የባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ፣ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር ትልቅ መደላድል ፈጥረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ አድማስ ይበልጥ አስፍተውታል። የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ራዕይ ለዓለም ያሳየችበት አጋጣሚ ነው።ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የካንሰር ህመምንና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ መለየት የሚያስችሉ የኤአይ ውጤቶችን አበልጽጓል። በግብርናውም ረገድ የአፈርን ለምነትና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ዋስትና ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል ዓለም ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የፋይዳ (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን መረጃ በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የለውጡ ፍሬያማነት ማሳያ ነው።የሳይንስ ሙዚየምም የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያሳይና የሀገሪቱን ቴክኖሎጂ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ሆኗል።የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቅርቡ መጠናቀቁ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2025 ስትራቴጂው መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዲጂታል 2030ን ይፋ ሲያደርጉ የነበረው ትልቁ መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች የሚል ነው። ስትራቴጂው በዋናነት"የፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት፣ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠር፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) አድርጎ መገንባትን እንደ ዋነኛ ግብ አስቀምጧል። ይህም ሁሉን አቀፍ የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ የመንግስት አገልግሎቶችን መቶ በመቶ ወረቀት አልባ በማድረግ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) በግብርና፣ በጤናና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ በስፋት በመተግበር የምርታማነት አብዮት መፍጠርን ያለመ ነው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ስራ በአህጉራዊ ደረጃ ያለውን ተቀባይነትና የተሰጣትን ትልቅ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት የቴክኖሎጂ ከፍታ፣ ሀገሪቱን በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ተፎካካሪ ብቻ ሳይሆን የፈጠራ ምንጭ እንድትሆንም እያደረጋት ይገኛል። በዚህ ረገድም የቀጣዩ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ስኬትም ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና በቴክኖሎጂ የበለጸገች ሀገር የማድረግ ራዕይን ለማሳካት እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ ያገለግላል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 3, 2026 315
ክልሎች፤ሚያዝያ 25/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮች በወፍ በረር ሲቃኙ ይህንን ይመስላሉ!!! 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡትን የቶዮ ሶላር ኢነርጂ ምዕራፍ ሁለት፣ የኦሪጂን እና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካን በይፋ መርቀዋል። እነዚህ የሶላር ፋብሪካዎች በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን፣ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅን እና 7 ቶን ሃይድሮጅን ለገበያ ያቀርባል። ‎ይህ ክንውን የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ለማፋጠን፣ የኢነርጂ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ዘላቂ፣ የማይበገር ሁለንተናዊ እድገት ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል። 👉እንቁላልን ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት የማቆየት ልምምድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ፤ የዶሮ እንቁላል ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት ያህል ማቆየት የሚያስችል ቴክኖሎጂን ወደ ተግባር ለማስገባት ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል። በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ሕክምናና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ማስተዋል ብርሃን፤ ዩኒቨርሲቲው የእንቁላል ምርት ብክነትና ብልሽትን ለማስቀረት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። በዚህም እንቁላልን እስከ ሁለት ዓመት ያለ ምንም ብልሽት ማቆየት የሚያስችለውን ቴክኖሎጂን የማላመድና የማስተዋወቅ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂው በአንድ ሊትር ውሃ ውስጥ 30 ግራም የኖራ አፈር ወይም ላይም ስቶን ጨምሮ በማዋሃድ እስከ 12 እንቁላሎችን ሳይበላሽ የሚያስቀምጥ በመሆኑ ለአርሶ አደሩ ተመራጭ ነው ያሉት። ይህም እስካሁን ባለው አንድ ትኩስ እንቁላል ሳይበላሽ መቆየት የሚችለው እስከ ሁለት ሳምንት መሆኑን ጠቁመው ቴክኖሎጂው ይሄን ችግር በመሰረታዊነት የሚቀይር ነው።፡ ቴክኖሎጂውን በስፋት በማስተዋወቅና በማላመድ ረገድም ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን በመስጠት ችግር ፈቺነቱን የማሳየት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። 👉የአፋር ጥጥ ተስፋ ሰጪ ፀጋ! የአፋር ክልል የበርካታ የተፈጥሮ ፀጋዎች ባለቤት ነው፤ ሆኖም እነዚህን እምቅ ሀብቶች ወደ ልማት በመቀየር ከፀጋዎቹ ተቋዳሽ ለመሆን ሳይቻል ለረጅም ተቆይቷል። አሁን ግን ከፀጋዎቹ አንዱ የሆነውን ተፈጥሯዊ ጥጥ (Organic Cotton) ለማምረት ተስፋ ሰጪ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በሰመራ በተካሄደ የውይይት መድረክም በግብርና ሚኒስቴር የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳምሶን አሰፋ፤ የአፋር ክልል ጥጥን በመስኖ ማልማት የሚቻልበት አቅም ያለው በመሆኑ ልማቱን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሀገራችን የጥጥ ልማትን ለማስፋፋት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው፤ ባለፈው የምርት ዘመን እንደ ሀገር በስድስት ክልሎች 110 ሺህ ሄክታር መሬት በጥጥ መልማቱን ተናግረዋል።በዚህም 79 ሺህ ሜትሮክ ቶን የተዳመጠ ጥጥ በማምረት ለኢንደስትሪዎች ማቅረብ እንደተቻለ ነው የገለፁት። 👉የሸማቹ ሸክም ይቀላል! የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ስድስት ከተሞች ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ ሲያካሄድ የህብረት ስራ ማህበራት ከእንግዲህ የሸማቹን ሸክም ሊያቀሉ ይገባል የሚል ሀሳብ ተነስቷል። በሀዋሳው በተካሔደው የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለያዩ መስኮች የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊት ሀገር ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን አንስተዋል። በተከናወኑ ተግባራትም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አክለዋል። የመንግስትን፣ የግሉ ዘርፍንና የዜጎችን የካፒታል አቅምና ዕውቀትን ደምረው የያዙት የህብረት ስራ ማህበራት ግብርናውን በማሻገር የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት በመቀየር ረገድ ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልፀው የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመፍታትና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር የሸማቹን ህብረተሰብ ሸክም ያቀላሉ ተብሎ እንደሚታመንም አስረድተዋል። 👉ምርምር ለቀጣናዊ ትስስር በጅማ ዩኒቨርሲቲ "ቀጠናዊ ሰላምና ትብብር ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ባለችበት ቀጣና የሚታዩ ፍላጎቶችን ለማሟላትና ተግዳሮቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመፍታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ተነስቷል። በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጦሽኔ ቀጣናውን በልማት ለማስተሳሰር በሚደረግ ጥረት የትምህርት ተቋማቱ የጥናትና ምርምር ድጋፍ ከፍተኛ ሚና አለው ያሉ ሲሆን ለዚህም ተቋማቱ ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያሳድጉ እና ማህበራዊ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚያግዙ የፖሊሲ መነሻ ሀሳቦችን በጥናትና ምርምር እንዲያፈልቁ አሳስበዋል። የሚወጡ ጥናቶች በቀጣናው በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ እየተከሰቱ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሊሆኑ እንደሚገባ የተጠቀሰ ሲሆን ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን በመተግበር እያከናወነች ያለችው ተግባር በተመክሮነት ቀርቦ አድናቆትን አስገኝቶላታል። 👉ሻይ ቅጠል አሁን አሁን አርሶ አደሩ በተለያዩ ኢንሼቲቮች በሚከናወኑ የግብርና ልማት ትግበራዎች ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። በርካታ አርሶ አደሮች በሻይ ቅጠል ልማት ኢንሼቲቭ በመሰማራት ገቢን ከማሳደግ ባለፈ ለሌሎችም ሰፊ የስራ ዕድል እየፈጠሩ ይገኛሉ። በጅማ ዞን የሻይ ቅጠል ልማትን ከማስፋፋት ባለፈ የበያ ትስስር የመፍጠርና ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለፋብሪካ ለማቅረብ ለአርሶ አደሩ ግንዛቤ እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም፤ በዞኑ የሻይ ቅጠል ልማትን በኢኒሼቲቨን መልክ በመተግበር የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድል እየተፈጠረ ነው። ዘንድሮም ስራውን ለማስቀጠል በተመረጡ 6 ወረዳዎች በመጪው ክረምት የሚተከሉ 50 ሚሊዮን ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን ህዝብን በማሳተፍም ወደ 2 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬትን ለመሸፈንም ታስቧል። ጥቅሙ የገባቸው አርሶ አደሮችም የሰብል ልማቱን ለጊዜው ተወት በማድረግ በሻይ ቅጠል ልማት ላይ እየተሳተፉ እንደሆነ ይናገራሉ። በዞኑ የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አርሶ አደር ሲራጅ ሼክ ከድር በሻይ ቅጠል ልማት ላይ መሳተፍ ከጀመሩ ወዲህ ገቢያቸው መጨመሩን ተናግረዋል። አርሶ አደር ሱልጣን አባሞጋ በበኩላቸው ተሰማርተውበት ከነበረው የሰብል ልማት ወደ ሻይ ቅጠል ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአካባቢ ፀጋን ተገንዝቦ ወደ ስራ መግባት ተጠቃሚነትን እንደሚያመጣ ማሳያ ሊሆን ይችላል። 👉ተስፋዎች ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በሆሳዕና ከተማ የተካሄደው የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ደረጃ ሽግግር እውቅና መርሃ ግብር ይጠቀሳል። "የኢንተርፕራይዞች ሽግግር ለእመርታዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ የተከናወነው የዕውቅና መድረክ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት ነው የተካሄደው። እሳቸው እንደገለፁት፤ ኢንተርፕራይዞቹ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ ነው። በክልሉ በገጠርና በከተማ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ ከ25 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ መስኮች መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በጥቃቅንና በአነስተኛ ደረጃ የሚገኙ 4 ሺህ 948 ኢንተርፕራይዞችን የማሸጋገርና 495 ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን የመለየት ስራ መሰራቱም እንዲሁ። ከኢንተርፕራይዝ ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሸጋገሩ አምራቾች እንደተናገሩት ሽግግሩ ስራቸውን በተሻለ ሁኔታ ለመከወን እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል። 👉ትምህርትና አርብቶ አደሩ የወፍ በረር ቅኝታችንን ስንቀጥል ጋምቤላ እንደርሳለን፤ በሳምንቱ በጋምቤላ ከተማ በተካሄደ መድረክም የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውም ተመልክቷል። በለውጡ ዓመታት የአርብቶ አደሩን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ውጤት መመዝገባቸውም እንዲሁ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም ረገድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና የገዘፈ መሆኑም በመድረኩ መገለፁን ቅኝታችን ዳሶታል። 👉ልወቅሽ ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ጠቅለል አድርጎ የዳሰሰው ቅኝታችን ደግሞ በስድስት ከተሞች ለማካሄድ ዕቅድ የተያዘለትና እስካሁን በጅማ፣ በሀዋሳና በደብረ ብርሃን ከተሞች የተካሄደው የ"ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ታላቁ ሩጫ" ከተሞቹን ከማስተዋወቅ የዘለለ ፋይዳውን በመርሃ ግብሩ ላይ በተላለፉ መልዕክቶቹ አሳይቷል። ለአብነት በጅማ የተካሄደው ‘ፖሊዮን በጋራ እናጥፋ’ የሚለውን የጤና ጉዳይን ያነሳ ነበር። በአዳማ ከተማ የተከናወነው ሁነት ደግሞ በመኪና ውድድር ታጅቦ የተከናወነና የቱሪዝም መስህቦችን ማስተዋወቅን ታላሚ ያደረገ ነበር። ‘’ለሀዋሳ ከፍታ እንሮጣለን’’ በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ሁነትም ከጅማና አዳማው ሁነት የተለየ እሳቤንም ሆነ መልዕክትን አልያዘም። ሁሉም ሁነቶች ከዋነኞቹ አምስት ምጣኔ ሃብታዊ አምዶች መካከል አንዱ የሆነውን ቱሪዝም ልማት በማጠናከር የማህበረሰቡን የዘርፉ ተጠቃሚነት ማላቅን ታሳቢ ማድረጋቸውን መመልከት ተችሏል። ቅኝቶቻችን በወፍ በረር ይህንን ይመስላሉ!! የሳምንት ሰው ይበለን!!!
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 26, 2026 692
ክልሎች፤ሚያዝያ 18 /2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር የምንቃኝበት ነው። በዚህ ሳምንትም አንኳር የክልሎች ክንውኑን የሚያሳዩ መረጃዎች ቀርበዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተም! ኢትዮጵያ የበጋ መስኖ ልማት ስራ መደባኛ ስራዋ ካደረገች ወዲህ አያሌ ለውጦች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ባለፉት ዓመታት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በእቅድ እና በቁርጠኝነት በመከናወኑ ከውጪ የሚገባ ስንዴ ቀርቷል፤ የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጥረቱም ቀጥሏል። ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚደረገው ሽግግርም ዓመቱን ሙሉ በማልማት እየታጀበ ሲሆን የአንበሳውን ድርሻ የሚይዘው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሥራ ነው። በዚህ ውስጥ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አበረታች ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በተያዘው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ወሬርሶ ማሊማ፣ በጂዳ ወረዳ ሲባ ሲርቲ እና ቂምቢቢት ወረዳ ሰገሌና ደርማሙሳ ቀበሌ በኩታ ገጠም የለማ እና በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ የስንዴ ቡቃያ አስቃኝተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፎቶ ጋር ያያዙት መልዕክትም ''ይህ የበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት በምግብ ራስን የመቻል እና የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተማችን ነው'' ይላል። ብሪክስ -- ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በባህር ዳር ከተማ ''የብሪክስ አሁናዊ አቅሞች እና የኢትዮጵያ የልማት ትብብር ትኩረቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ጉባኤ አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ በመሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑ ይታወቃል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሐመድራፊዕ አባራያ በመድረኩ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ሳትፎዋን በማሳደግ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የተደራጁ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። መድረኩም ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችላት የሁለትዮሽ ትብብር ጭምር የተካሄደበት፤ በብሪክስ ማዕቀፋ በተለይም በግብርና እና ስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና መሰል ዘርፎች ልምድ የተሰጠበትም መሆኑ ተመላክቷል። ማረም እና ማነጽ የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል እንዲሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት መሰጠቱ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነው። የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነሮች የጋራ ጉባኤ “የማረሚያ ተቋማት ለሀገር ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል ሆነው እንዲያገለግሉ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከታራሚዎች የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የመሰረታዊ ፍላጎት አቅርቦት፣ ከማረሚያ ቤት የሪፎርም ሥራዎች እንዲሁም ከማረም የማነጽ ተሃድሶ ልማት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ጉባኤው በልዩ ሁኔታ የመከረበት ነው። ኢትዮጵያ ማምረቷን ቀጥላለች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የራስን አቅም የመገንባት ታሪካዊ ጉዞ እንደቀጠለ ነው። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል "ድሬ ታምርት ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ በተዘጋጀ የአምራች ኢንዱስትሪ ኤክሲፖ ላይ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ በተደረገው ድጋፍና ክትትል እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በንቅናቄው የተዘጉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲመለሱ በማድረግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በጥራትና በስፋት እየተተኩ ነው ብለዋል። ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድም መሠረታዊ ውጤቶች ተገኝተዋል ነው ያሉት። ዘንድሮ ብቻ 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ የውጭ ሀገራት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት መዘጋጀታቸውም ተገልጿል። ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል በኢትዮጵያ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ውኃ የህልውና ጉዳይ ነው። በእርግጥ ለፍጡራን ሁሉ ውኃ ህይወት ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ግን ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል። በሳምነቱም በአፋር ክልል ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የአይሳኢታ አፋምቦ የብዙሃን መንደር እና የአይሳኢታ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተከናወነው ልማት የህብረተሰቡን ጥያቄዎች በተግባር ከመመለሱ በላይ፣ በየደረጃው ያለውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፤ መንግስት የውሃ ሽፋን አነስተኛ ለሆነባቸው አካባቢዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት፣ በፕሮጀክቶች ታግዞ መስራት እንደሚገባ በጽኑ ያምናል፤ በተለይም የለውጡ መንግስት ለቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች በሰራው ስራ የውኃ ተደራሽነት በእጅጉ ማደጉን አንስተዋል። ልምድ ልውውጥ እና ተሞክሮ -ለምክር ቤቶች ሌላው ቅኝታችን በዚህ በተጠናቀቀው ሳምንት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤትና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ መካሄዱን የዳሰሰ ነው። የጋራ የምክክር መድረኩ ዓለማ የልምድ ልውውጥና የልማት ሥራዎችን በመመልከት ተሞክሮ መለዋወጫ ነው።የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ፤ መንግስት ሕዝቡ የሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የምክር ቤቶችን አደረጃጀት ማጠናከርና የክልሉ ሕገ መንግስት ያስቀመጣቸውን ኃላፊነቶች መፈጸም ይገባል ብለዋል።የመንግስት የልማት ኢኒሼቲቮች የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል የሚያስችሉ በመሆናቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መተግበር እንዲችሉ ምክር ቤቶች ያለሰለሰ ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተመልክቷል። የጤና ልማት ስራ እስከ አክሞ ማዳን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ በሚደረግ ጥረት የአጋር ድርጅቶች አስተዋጾ ትልቅ ድርሻ እንዳለውም የተመለከተው በዚህ ሳምንት ነው። ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጋር በመሆን በአርባ ምንጭ ከተማ ያስገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ መሰል የጤና ዘርፍ የልማት ስራዎች መንግስት በዘርፉ የያዘውን ውጥን ከማሳካት አንጻር እገዛቸው ትልቅ መሆኑን አንስተዋል።ማዕከሉ ማህበረሰቡ በቅርበት ሕክምና እንዲያገኝ ከማስቻል ባለፈ ወደ ሌላ አካባቢ ሄዶ ሲታከም ሊያወጣ የሚችለውን ወጪ ያስቀራል። ማዕከሉ የኩላሊት እጥበት ማሽኖች፣ የመድሃኒት ቤት፣ መኝታ አልጋዎችና የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሟልቶ የተገነባ መሆኑም ታውቋል። የከተሞች ኮሪደር- ከቱሪዝም እስክ ኮንፍረንስ ማዕከልነት በኮሪደር ልማት እጅግ ከተዋቡ እና ከደመቁ የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል ሀዋሳ አንዷ ናት። በሳምንቱ የከተማዋ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ማጠናቀቂያ የምስጋናና ዕውቅና እንዲሁም የአራተኛ ዙር የኮሪደር ልማትና የሐይቅ ዳርቻ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄዷል፡፡ የሲዳማ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርቡ ቀጥሏል ብለዋል። በቀጣይ ለሚከናወነው የኮሪደር እና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ስራዎች እንደሚቀጥሉ አንስተው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጎላ መሆኑን ገልፀዋል። የከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነት ለማጠናከር ሥራዎች በላቀ ፍጥነትና ጥራት መከናወናቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ምርጫ -የዴሞክራሲ መሰረት ሳምንቱ በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ከመጠናቀቁ በፊት መራጮች የምርጫ ካርድ ወስደው ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹበትም ነበር። ኢትዮጵያዊያን መጪውን ጊዜ የተሻለ የሚያደርግላቸውን መንግስት ለመመረጥ ዝግጅታቸውን በተግባር እያረጋገጡ ነው።
ትንታኔዎች
የ471 ሚሊዮን ተከታዮች ባለቤት የሆኑ የ30 ሀገራት ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሳተፉበት ታሪካዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ
May 6, 2026 349
በመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) ላይ ለመሳተፍ፣ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡና በአጠቃላይ 321 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 61 ታዋቂ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ወደ አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። እነዚህንም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 120 ታዋቂ ኢትዮጵያውያን የማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ፈጣሪዎች ይቀላቀሏቸዋል። ታሪካዊው ጉባኤ ነገ እና ከነገ በስቲያ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ጉባኤው በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እና በኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ የጋራ ትብብር የተዘጋጀም ነው። በአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከል አዲስ አበባ የሚካሄደው ይህ ጉባኤ የአፍሪካን ዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ እንደገና ለመቅረጽ ያለመ ነው። ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበር እና የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅበት ስም ነው) ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገብቷል። ሴራሊዮናዊው ቦይዜ ክሪሽ፣ ቤኒናዊቷ ሬጌ ቦይዘር፣ ሴኔጋላዊው ጃው ኬቹፕ እና ስዊዛላንዳዊው ጎጎ እስዋቲኒ ኤምኤም ሌሎች ለጉባኤው የገቡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖፐ ፈጣሪዎች ናቸው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎቹ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል። ጉባኤው በአፍሪካ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሰባሰቡበት፣ ስለራሳቸውና ስለ አፍሪካ የሚናገሩበት፣ እንዲሁም ስለ ይዘት ፈጠራና ስለሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች የሚወያዩበት መድረክ ነው። ይህም ተጽእኖ ፈጣሪዎቹን በአንድ መድረክ የማገናኘት ትልቅ አጋጣሚን ፈጥሯል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በመጠቀም የይዘት ፈጣሪነት የወደፊት ሁኔታ፣ የአፍሪካ አዎንታዊ ገጽታን መገንባት እና የዲጂታል ተጽዕኖን ከአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ጋር ማጣጣም በሚሉ ጉዳዮች ላይ ሶስት የከፍተኛ ደረጃ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ጉባኤው "በችግር ላይ የተመሰረተ" ዘገባን በእውነተኛ የአፍሪካ የዕድገት ታሪኮች ለመተካት የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑም ተመልክቷል። የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ የኢትዮጵያን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ የማስተዋወቅ እድሉ ሰፊ ነው። እነዚህ የይዘት ውጤቶች የአፍሪካን መልካም ገጽታ ለዓለም፣ የኢትዮጵያንም መልካም ገጽታ ለአፍሪካውያን ማሳየት የሚችሉ ናቸው። ጉባኤው ሐሙስ ዕለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚጀመር ሲሆን፣ ከ470 ሚሊዮን በላይ የዲጂታል ተከታዮች አይኖች በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ላይ አርፈዋል። ይህም አፍሪካ የራሷን ታሪክ ራሷ መተረክ የጀመረችበት አዲስ ዘመን ማሳያ ሆኗል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 2, 2026 652
ከሚያዝያ 18 እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአዲስ አበባ በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘውን "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የጎበኙ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ይህ ፋብሪካ በ2025 ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ያድርጉ ፎረም (Invest in Ethiopia Forum) አማካኝነት በተፈረመው ስምምነት መነሻ በ100 ሚሊየን ዶላር የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የተቋቋመ ነው ብለዋል። ‎በውጤታማ ድጋፍ እና ክትትል በስድስት ወራት ብቻ እውን የሆነው "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻ ዘመናዊ ማሽኖች እና በቴክኖሎጂ የተዋቀረ መሆኑን ገልጸው፣ ማምረቻው ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድልም ፈጥሯል ነው ያሉት። ‎በመጀመሪያ ምዕራፍ 2 ጌጋዋት ዓመታዊ የማምረት ዐቅም ያለው ፋብሪካው የኢትዮጵያን የኃይል ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ከታዳሽ ኃይል ለማድረግ ለተጀመረው ሀገራዊ ርዕይ እውን ለማድረግ ተደማሪ ዐቅም ፈጥሯል ሲሉም ተናግረዋል። በተጨማሪም በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ የሚገኘውን የጫማ ማምረቻ እና ንዑስ የኤሌክትሪክ ጣቢያን ተመልክቻለው ብለዋል በመልዕክታቸው። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአራዳ ፓርክን መመረቃቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት አራዳ ፓርክን በመረቁበት ወቅት፤ ፓርኩ አዲስ አበባን ለመለወጥ ያለንን ርዕይ በተግባር ያሳየንበት አንዱ ሥራችን ነው ብለዋል። ቀደም ሲል ተዘንግቶና ለአደጋ ተጋልጦ የነበረው የአራዳ አካባቢ፤ ዛሬ ተመልሶ ተገንብቶ አስደናቂ የከተማ አካል መሆን ችሏል ሲሉም ገልጸዋል። ‎ኢትዮጵያ ለእኛ በምናብ የምትሳል ህልም ብቻ ሳትሆን በተግባር የምትገነባ እውነታ ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጤናማ፣ ጽኑ፣ ለመጭው ትውልድ ተስፋን ከተጨባጭ ሀብት ጋር የምትሰጥ፣ በአፍሪካ መሪ፣ በዓለም መድረክ ደግሞ ተወዳዳሪ የሆነች ሀገር እየገነባን እንገኛለን ብለዋል። በየቀኑም ተስፋን ወደ እውነታ የመለወጥ ተግባራችንን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል። • ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ሐሳባቸውን ያጋሩበት “የማኅበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀውና በማኅበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የቀረቡበት የምክክር መድረክ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‎የማኅበራዊ ዘርፍ ግንባታ እንደ ሌሎች መሠረተ-ልማቶች ውጤቱ ወዲያው የሚታይና የሚጨበጥ ባይሆንም፤ ለሀገር ዘላቂና ወሳኝ መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በሚገጥሟት ተግዳሮቶች ሳትገደብ ከሚገመተው በላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተገነባች መሆኗን ገልጸው፤ ምንም እንኳ የዐቅም ውስንነቶች ቢኖሩብንም ለማሻሻል ያልተሞከረ የማኅበራዊ ዘርፍ የለም ሲሉም አስረድተዋል። ‎በየዘርፎች የታለመው ሁሉ በተግባር እንዲተረጎምና ተገቢውን ዓላማቸውን እንዲያሳኩ ብዙ ሥራ ይጠበቅብናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም አንድ እጅ ብቻውን ማጨብጨብ እንደማይችል ሁሉ፤ መንግሥት የሚጀምራቸውን ሥራዎች ሌላው የማኅበረሰብ ክፍል እንደ አንድ ባለ ድርሻ ኃላፊነት ወስዶ በጋራ መቆም እንዳለበት አስገንዝበዋል። • የሞዛምቢክ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት የሞዛምቢክ ፕሬዚዳንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በክብር ተቀብለዋቸዋል። የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጋራ ልማትና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ትርጉም ባለው መልኩ ሊለውጡ የሚችሉ ተጨባጭ ሥራዎችን ቅድሚያ የሰጠ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለእውነተኛ አፍሪካዊ አጋርነት ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ መሆኑንም አስረድተዋል። ከዚያም ባደረጉት ቆይታ ዘላቂ እና ተጨባጭ ለውጥ ለሚያመጣ አጋርነት መሠረት የጣለ ፍሬያማ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በስትራቴጂካዊ ዘርፎች ያለንን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩና የአሠራር ማዕቀፍ የሚሆኑ ልዩ ልዩ የመግባቢያ ሠነዶችን ልውውጥ አካሂደናል ብለዋል። • የበጋ መስኖ እርሻ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የበጋ መስኖ እርሻ በምግብ ራሳችንን ለመቻል በሚደረገው ጉዞ ውስጥ የጸና መሠረት የጣልንበት ምዕራፍ ነው ብለዋል። ‎የውኃ ሀብታችንን በአግባቡ በመጠቀም፣ ባልተቋረጠ ጥረት እና ቁርጠኝነት፣ የመልማት ጉዟችን አስተማማኝና ዘላቂ የሆነ የምግብ ዋስትና ወደምናረጋግጥበት ብሩህ ተስፋ እንደሚያሸጋግረን ጥርጥር የለውም ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሆሞሻ ወረዳ የሚገኘውን ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት ጎብኝተዋል። ጉብኝታቸውን ተከትሎም፤ ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት በኢትዮጵያ የግሉን ዘርፍ ያሳተፈ የግብርና ሥራ እንዲስፋፋ ለሚደረገው ሥራ አንድ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ በግል ባለሀብት እየለማ ያለው የግብርና ሥራ እንደ ሶላር ያሉ የኃይል አማራጮችን እና የከርሰ ምድር ውኃን በመጠቀም በመስኖ በማልማት ኢትዮጵያ ለጀመረችው የግብርና ልማት እና የገጠር ሽግግር ሰፊ አስተዋጽኦ ያበረክታል ሲሉም ገልጸዋል። በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግራናይት የሚያመርተውን የኦርላመንት (3ኤም) ማርብልና ቴራዞ ማኑፋክቸሪንግ የሥራ እንቅስቃሴ የጎበኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት የግሉ ዘርፍ በማዕድን ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፍ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ፣ ማበረታቻና ድጋፍ እንዲህ ያሉ ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ ነው ብለዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከወርቅ እስከ ግራናይት በተፈጥሮ የታደለ መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ፀጋ ለሀገር ብልጽግና ለማዋል የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ይበልጥ እንዲጠናከሩ የፌደራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 745
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። ‎አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። ‎በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ‎የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (‎5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (‎ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ‎‎ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። ‎‎የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ጤና ከሀገር በቀል ስኬት ወደ አህጉራዊ መሪነት
Apr 23, 2026 691
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ እያከናወነች ያለችው ስራ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂካዊ የሆኑ ተቋማዊና የፖሊሲ መሰረቶች ተጥለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መቋቋም ለሀገራዊ ችግሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ መፍትሄ ለማግኘት ትልቅ አቅም የፈጠረ ሲሆን፣ ብሄራዊ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ ተቀርጾ መጽደቁ ደግሞ የዘርፉን ልማትና አጠቃቀም በተደራጀ መንገድ ለመምራት አስችሏል። እነዚህ እርምጃዎች ሀገሪቱ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እና 2030 ስትራቴጂ ውስጥ ቴክኖሎጂውን እንደ ቁልፍ የለውጥ አቅጣጫ እንድትጠቀም በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ዘላቂ ለማድረግም በሰው ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በኮዲንግ፣ በዳታ ሳይንስ እና በክህሎት ለማሰልጠን የተጀመረው ግዙፍ ፕሮግራም የለውጡ አንቀሳቃሽ ኃይል እየሆነ ነው። ከዚህም ባለፈ፣ በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ እንዲገነባ መታቀዱና በዚህ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባልነት ውስጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት እንዲሳተፍ መወሰኑ፣ ሀገሪቱ ቴክኖሎጂውን ለውሳኔ ጥራትና ለምርምር በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀመችበት መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ እንደገለጸው፣ ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በሹመት ደብዳቤው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ AI ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አክሎ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የAI አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል እና በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ለሀገራዊ ለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ በዝርዝር አስፍሯል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የAI ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የተያዘው ሥራ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክርም ተገልጿል። ይህ አህጉራዊ እውቅና በተለይ በጤናው ዘርፍ የታዩ ውጤቶችን ያካትታል። ኢትዮጵያ በኤአይ የታገዘ ዲጂታል ኤክስሬይን ለሳንባ ነቀርሳ ምርመራ ካዋሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። በተጨማሪም የ"HEP Assist" መተግበሪያን በሙከራ ደረጃ በማስጀመር፣ በገጠር የሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ውስብስብ ምልክቶችን ሲያዩ ሙያዊ የሕክምና ውሳኔ እንዲሰጡ ድጋፍ እየተደረገ ነው። እነዚህ የዲጂታል ጤና ስራዎች በ7 ክልሎችና በ15 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ መጀመራቸው፣ ቴክኖሎጂው በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የአገልግሎት ልዩነት ለማጥበብ ያለውን ፋይዳ ያሳያል።   በአጠቃላይ፣ የኤአይ ቴክኖሎጂ በጤናው ዘርፍ ከሚሰጠው የጡት ካንሰር፣ የአንጎል እብጠትና የቆዳ በሽታዎች ምርመራ ባለፈ፣ በግብርና፣ በፋይናንስና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥም በስፋት እየገባ ይገኛል። በ2030 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ሆስፒታሎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል አገልግሎት ለመቀየር የተቀመጠው ግብ፣ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የጀመረችውን የቴክኖሎጂ ነጻነትና የመሪነት ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓት በጤና፣ በግብርና እና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በጤናው ዘርፍ እንደ ካንሰር እና ሳንባ ነቀርሳ ያሉ በሽታዎችን ቀድሞ በመለየት የህክምና ጥራትን ሲያሻሽል፣ በግብርናው ደግሞ የሰብል ተባዮችንና የቡና በሽታዎችን በመለየት ምርታማነትን እያሳደገ ነው። ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂው በመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ እና በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ሰፊ የመረጃ ትንታኔዎችን በፍጥነት በማከናወን፣ የሥራ ፍጥነትን እና የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል። የዘርፉ ፋይዳ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባለፈ የሀገሪቱን የዲጂታል ሉዓላዊነት እና የሰው ኃይል አቅም በመገንባት ላይ ያተኩራል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶችን በኮዲንግ እና በዳታ ሳይንስ በማሰልጠን እንዲሁም የፈጠራ ማዕከላትን (Startups) በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በሌሎች ላይ ጥገኛ ከመሆን ወጥታ የራሷን የዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ይህም በአህጉር ደረጃ ለሚደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች እንደ አርአያ በመሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ ፍትሃዊነት የመጠቀም ጥቅል ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አድርጎታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሹመት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ ያጎላል። በተጨማሪም ሹመቱ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና አፍሪካ በኃላፊነትና በፍትሐዊነት በታጀበ የኤአይ አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንድትሆን የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣም ያደርጋታል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 4683
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 3093
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8885
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 7369
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 62354
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 55751
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 36222
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33825
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 28415
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27746
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 27239
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26709
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 62354
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 55751
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 36222
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33825
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 977
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው።   በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል።   የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል።   የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል።   ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 997
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም