ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ከ27 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ተደርገዋል -ኢመደአ
Feb 8, 2026 18
አዲስ አበባ፣ የካቲት 1 /2018 (ኢዜአ) ፦የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) በስድስት ወራት ከተሞከሩ 27 ሺህ 773 የሳይበር ጥቃቶች 99 ነጥብ 03 በመቶ የሚሆነውን ማክሸፍ ተችሏል አለ። ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሂዷል። የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተቀያየሩ የመጡትን የሳይበር ጥቃት ባህሪያት ግምት ውስጥ በማስገባት የመከላከል አቅማችን እየዘመነ ይገኛል ብለዋል፡፡ የሳይበር ደህንነት ሥጋቶችን ቀድሞ ለመለየትና ምላሽ ለመስጠት የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶችን ለማበልጸግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራተጂ መሠረት የሚሆኑ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው የመንግሥት ተቋማትን ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ አሠራራቸውን ዲጂታላይዝ የሚያደርጉ የቴክኖሎጂዎችን እንዲታጠቁ መደረጉን ገልጸዋል። ለአብነትም ገቢዎች ሚኒስቴር የኢ-ኢንቮይስ፣ አዲስ አበባ ገቢዎች የሰውነት ላይ ካሜራ፣ እንዲሁም ፌደራል ፖሊስ የተቀናጀ የሰው ሀብትና የሰነድ አስተዳደር ሲስተሞችን በማልማት አገልግሎታቸውን እንዲያዘምኑ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የሚሰነዘሩ የሳይበር ጥቃቶችን ለማክሸፍ እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ በስድስት ወራት ከተሰነዘሩ 27 ሺህ 773 የሳይበር ጥቃቶች ውስጥ 99 ነጥብ 03 በመቶ የሚሆነውን ማለትም 27 ሺህ 505ቱን ማክሸፍ መቻሉን ገልጸዋል። የዲጂታል ፎረንሲክ ምርመራን በተመለከተ አስተዳደሩ ከቀረቡለት 253 የምርመራ ጥያቄዎች ውስጥ ለ245ቱ ምላሽ መሰጠቱን የኢመደአ መረጃ አመልክቷል፡፡ የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች ፦ https://linktr.ee/ENADigital
የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋን የቱሪዝም መስህብነት አሳድገዋል
Feb 8, 2026 59
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):-በመዲናዋ የተገነቡ የኮሪደር ልማትና ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋን የቱሪዝም መስህብነት ማሳደጋቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ቱሪዝም ኮሚሽን ገለጸ። "ብስከሌትን በአዲስ" በሚል መሪ ሃሳብ የብስክሌት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ እየተካሄደ ይገኛል። የአዲስ አበባ ከተማ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ቢንያም ታዬ ፤ የቱሪዝም ዘርፍ የዓለም ዋነኛ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ኢንዱስትሪ መሆኑን ገልጸዋል።   ዘርፉ ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል ፈጠራ፣ ለውጭ ንግድ፣ ለኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እና ጥቅል ሀገራዊ ምርት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሀገሪቱን ፈርጀ-ብዙ የቱሪዝም ሃብቶች በስፋት በማልማት ተገቢውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲያስገኝ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። በአዲስ አበባ በኮሪደር ልማትና ወንዝ ዳርቻ የተገነቡ መሰረተ ልማቶች የዚሁ አካል መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይህም የከተማውን ገጽታ የቀየሩና የቱሪዝም መዳረሻዎችን ያሳደጉ ናቸው ብለዋል። የብስክሌት ፌስቲቫሉ በየወሩ የሚከናወን መሆኑን አንስተው ዓለማውም ከተማዋ ያሏት መዳረሻዎችን ለማስተዋወቅና ግንዛቤ ለመፍጠር ነው ብለዋል።   በከተማዋ ኮሪደር ልማትና በወንዝ ዳርቻ የተገነቡ ውብና ሳቢ የሆኑ የቱሪዝም መዳረሻዎች ብስክሌትን እንደ አማራጭ የትራንስፖርት መገልገያነት ተጠቅመው መጎብኘት እንደሚቻል ለማስገንዘብ እንደሆነም አመላክተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አስመሮም ብርሃኔ በበኩላቸው፤ በከተማዋ ሞተር አልባ ትራንስፖርት ለማስፋፋት እየተከናወኑ ከሚገኙ ስራዎች መካከል የብስክሌት ትራንስፖርት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አካባቢ ተፈጥሯዊ ፣ ውብና ሳቢ ገጽታውን ጠብቆ እንዲቆይ ትልቅ አበርክቶ ያለው ነው ብለዋል።
በክልሉ የፋይናንስ ስርአቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል እየተሰራ ነው
Feb 8, 2026 36
ከሚሴ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):- በአማራ ክልል የፋይናንስ ስርአቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠንና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በከሚሴ ከተማ እያካሄደ ነው። የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን እንደገለፁት፣ የክልሉን ገቢና ወጭ በማጣጣም ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው።   ለዚህም የፋይናንስ አጠቃቀምን ዲጂታላይዝ በማድረግ በሀብት አጠቃቀምና በሌሎችም አበረታች ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል። በተለይም በመንግስት ግዥ፣ በውስጥ ኦዲት፣ በወጪ አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጡ ግልጸኝነት ያለው አሰራርን በመዘርጋት ለክልሉ ዘላቂ ልማት እንዲውል አግዟል ብለዋል። በክልሉ የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ ለውጡ የፋይናንስ ተቋማትን ማዘመኑ ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደር ልማት ላይ እንዲውል አስችሏል ብለዋል።   በዚህም በዞኑ የተለያዩ የበጀት ምንጮችን በአግባቡ በመጠቀም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል። የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሀብት፣ ንብረትና ግዥ አሰራሩን ማሻሻል ተችሏል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሰላማዊት ነጋ ናቸው። ገንዘብ በአግባቡ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የተጠናከረ ቁጥጥር እየተደረገ ነውም ብለዋል። የሰሜን ጎጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ አቶ በላይነህ ወንድም አፈራሁ በበኩላቸው፣ የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ መቻሉ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስችሏል ብለዋል።   ከዚህ በተጨማሪም ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ለህብረተሰቡ ተአማኒነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚካሄደው መድረክ ላይም የክልሉና የዞን አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
ከመሬት ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት የካዳርስተር ምዝገባ ዲጂታላይዝድ እየተደረገ ነው
Feb 8, 2026 32
ደብረ ብርሃን፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፡- ከመሬት ጋር ተያይዞ የሚነሱ የመልካም አሥተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የካዳርስተር ምዝገባ ዲጂታላይዝድ እየተደረገ መሆኑን የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር መሬት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ እታለማሁ ይምታቱ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በከተማዋ የመሬት መረጃዎችን በማዘመን አገልግሎት አሰጣጡን ዲጂታላይዝ እየተደረገ ነው ብለዋል። መሬትን በካዳስተር ሥርዓት መመዝገብ ገቢን ከማሳደግ ባለፈ ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል የጎላ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በያዝነው የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ከ7 ሺህ ለሚልቁ ባለይዞታዎችን ሕጋዊነት የማረጋገጥ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰዋል። ይዞታቸው የተረጋገጠ ከ2 ሺህ 800 በላይ መሬቶችን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ማስገባት መቻሉንም ጠቁመዋል።   በከተማዋ የጠባሴ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ፈለቁ ጌታነህ እና ጌታነህ ሸዋፈራ እንዳሉት፤ ዘመናዊ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ሕገ-ወጥነትን በመከላከል ፍትሐዊ አገልግሎት ማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ትኩረት ተሰጥቷል-ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
Feb 8, 2026 47
አዳማ፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፦ስፖርትን ለስነ ምግባር ግንበታና ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ያለውን እቅም ለማሳካት ትኩረት መሰጠቱን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለፁ። ሀገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች ስፖርት ስልጠና ምዘና ውድድር "የተተኪ ስፖርተኞች ልማት፤ ለስፖርታችን እድገት" በሚል መሪ ሐሳብ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ዛሬ ተጀምሯል።   የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በወቅቱ ስፖርትን ለስነ ምግባር ግንባታና ተተኪዎችን ለማፍራት ያለውን አቅም ለማሳካት ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ስፖርትን ለሀገር ገፅታ ግንባታና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ሚናን ለማጉላት እንዲቻል በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራትም የምልመላና ስልጠና ስርዓት ከመዘርጋት ጎን ለጎን ለስፖርት መሰረተ ልማት ተደራሽነት ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።   ባለፉት ስምንት ዓመታት 17 ሺህ 636 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በሀገሪቷ ተገንብተው ለታዳጊዎች የአካልና የአእምሮ ብቃት ማጎልበቻ አገልግሎት እንዲውሉ መደረጉን ገልጸዋል። ዛሬ በአዳማ የተጀመረው ውድድርም ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።   የኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ ሮዛ ቢያ እንደተናገሩት፥ ክልሉ ለስፖርት ልማት ዘርፍ ትኩረት በመስጠት ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው። የስፖርት ልማትን ለማሳካት የክልሉ ከተሞችና ወረዳዎች የስፖርት ማዘወተሪያዎችን ከኮሪደር ልማት ጋር በማቆራኘት እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ዛሬም በ15 የስፖርት አይነቶች ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡ ከ3ሺህ በላይ ታዳጊዎች በውድድር እየተሳተፉ ይገኛሉ ብለዋል።   የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው ከተማዋን ለነዋሪው ምቹ ለማድረግ የስፖርትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች እየተገነቡ ይገኛሉ ብለዋል። ታዳጊዎች በአእምሮና በአካል ብቁ እንዲሆኑ የመዝናኛና ስፖርት ስፍራዎች በከተማዋ በስፋት እየተገነቡ መሆኑን አስረድተዋል። የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች ፦ https://linktr.ee/ENADigital
የሚታይ
የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋን የቱሪዝም መስህብነት አሳድገዋል
Feb 8, 2026 59
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):-በመዲናዋ የተገነቡ የኮሪደር ልማትና ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋን የቱሪዝም መስህብነት ማሳደጋቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ቱሪዝም ኮሚሽን ገለጸ። "ብስከሌትን በአዲስ" በሚል መሪ ሃሳብ የብስክሌት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ እየተካሄደ ይገኛል። የአዲስ አበባ ከተማ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ቢንያም ታዬ ፤ የቱሪዝም ዘርፍ የዓለም ዋነኛ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ኢንዱስትሪ መሆኑን ገልጸዋል።   ዘርፉ ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል ፈጠራ፣ ለውጭ ንግድ፣ ለኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እና ጥቅል ሀገራዊ ምርት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሀገሪቱን ፈርጀ-ብዙ የቱሪዝም ሃብቶች በስፋት በማልማት ተገቢውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲያስገኝ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። በአዲስ አበባ በኮሪደር ልማትና ወንዝ ዳርቻ የተገነቡ መሰረተ ልማቶች የዚሁ አካል መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይህም የከተማውን ገጽታ የቀየሩና የቱሪዝም መዳረሻዎችን ያሳደጉ ናቸው ብለዋል። የብስክሌት ፌስቲቫሉ በየወሩ የሚከናወን መሆኑን አንስተው ዓለማውም ከተማዋ ያሏት መዳረሻዎችን ለማስተዋወቅና ግንዛቤ ለመፍጠር ነው ብለዋል።   በከተማዋ ኮሪደር ልማትና በወንዝ ዳርቻ የተገነቡ ውብና ሳቢ የሆኑ የቱሪዝም መዳረሻዎች ብስክሌትን እንደ አማራጭ የትራንስፖርት መገልገያነት ተጠቅመው መጎብኘት እንደሚቻል ለማስገንዘብ እንደሆነም አመላክተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አስመሮም ብርሃኔ በበኩላቸው፤ በከተማዋ ሞተር አልባ ትራንስፖርት ለማስፋፋት እየተከናወኑ ከሚገኙ ስራዎች መካከል የብስክሌት ትራንስፖርት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አካባቢ ተፈጥሯዊ ፣ ውብና ሳቢ ገጽታውን ጠብቆ እንዲቆይ ትልቅ አበርክቶ ያለው ነው ብለዋል።
ቀርጫንሼ ግሩፕ እና የብራዚሉ የግብርና ምርምር ተቋም የቡና ቴክኖሎጂ ስምምነት ተፈራረሙ
Feb 7, 2026 93
አዲስ አበባ፤ ጥር 30 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ቡና ላኪ ቀርጫንሼ ግሩፕ እና የብራዚሉ የግብርና ምርምር ተቋም በቡና ልማት እና ቴክኖሎጂ ዙሪያ በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል። የቡና ማምረት ስርዓቶችን በጋራ መቅረጽም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል። በስምምነቱ መሰረት በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ደበቃ ያለውን የቡና ምርት ማሻሻል ስራ ይከናወናል። የጥራት ደረጃ ስርዓቶችን ማሻሻል እና የግብርና ባለሙያዎችን አቅም መገንባት የስምምነቱ አካል ነው።   የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢፋ ሙለታ (ዶ/ር) ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አመልክተዋል። መንግስት የስምምነቱ ትግበራ ውጤታማ እንዲሆን እና የታለመለትን ግብ እንዲመታ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግም ገልጸዋል። የቀርጫንሼ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ እስራኤል ደገፋ ኢትዮጵያ እና ብራዚል በግብርናው ዘርፍ በርካታ መመሳሰሎች እንዳላቸው አንስተዋል። የስምምነት ማዕቀፉ የሁለቱን ሀገራት ትብብር የሚያጠናክርና ብራዚል በቡና ልማት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ያላትን ልምድ ለማካፈል መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር ተናግረዋል።   በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይ በኢትዮጵያ የብራዚል አምባሳደር ጃንዲር ፌሬራ ዶ ሳንቶስ እና የብራዚል የግብርና ምርምር ኮርፖሬሽን ፕሬዝዳንት ሲልቪያ ማሪያ ፎንሴካን ጨምሮ የመንግስት ባለስልጣናትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢትዮ-ብራዚል የኢኮኖሚ ትብብር ፎረም ትናንት የተካሄደ ሲሆን ሁለቱ ሀገራት በንግድ እና ግብርና ዘርፎች ያላቸውን ስምምነት ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶች መፈራረማቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በብልፅግና ጎዳና በፍጥነት እየገሰገሰች እንደምትገኝ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ቋሚ ምስክር ነው
Feb 7, 2026 93
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2018(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ በብልፅግና ጎዳና በፍጥነት እየገሰገሰች እንደምትገኝ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ቋሚ ምስክር ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ሐይቅ ከተማ የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት መርቀዋል። በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አፍላቂነት የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት የአከባቢውን ጸጋ በገለጠ መልኩ ለውጤት በቅቷል። የብልፅግና መንግሥት የማይሰራውን ቃል አይገባም፤ ቃል የገባውንም አይዘነጋም ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርትም በውጤታማነት መጠናቀቁ ለዚህ አብነት ነው ብለዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ኢትዮጵያ በብልፅግና ጎዳና በፍጥነት እየገሰገሰች ለመሆኑ ህያው ምስክር መሆኑንም አመልክተዋል። የመደመር መንግሥት ሀገረ መንግሥት ግንባታን የማሳካት ግብ ይዞ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ጠንካራ፣ የበለፀገች፣ የታፈረች፣ የተከበረች፣ ፍትሐዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ህብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን መገንባት በትኩረት እየሰራባቸው ካሉ ጉዳዮች መካከል መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህ ደግሞ የገበታ የልማት ፕሮጀክቶች ማሳያዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።   የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች ተጠናቅቀው ሀብት እያፈሩ ሕዝብ እያስተሳሰሩ መሆኑን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች የፕሮጀክት አፈጻጸም መመሪያዎች ሆነው እያገለገሉ መሆኑን አብራርተዋል። የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶችም ተከታታይነት ባለው መልኩ እየተመረቁ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ እያነቃቁ ነው ብለዋል።   ባለፉት የለውጥ ዓመታት የታየው የመሪ ቁርጠኝነት፣ ሀገር ወዳድነት፣ ለቃል መታመን፣ የመፍጠርና መፍጠን መርህን የተከተለ አካሄድ እንዲሁም ጀምሮ የመጨረስ ባህል መዳበሩ በሁሉም መስክ ውጤት እንዲመዘገብ መሰረት መጣሉን ገልፀዋል።
በትምህርት ዘርፉ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎችና የሥርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች ጥራትን በማስጠበቅ ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ ነው
Feb 7, 2026 114
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2018(ኢዜአ)፦ በትምህርት ሥርዓቱ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለመጠገንና ጥራትን ለማረጋገጥ የተከናወኑ የፖሊሲና የሥርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ደኤታ አየለች እሸቴ ገለጹ። በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርትን ከመሠረቱ የማስተካከልና የደረጃ ማሻሻያ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ በአጠቃላይ ትምህርት እና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከመሠረተ ልማት ማሻሻያ ጀምሮ የትምህርት ጥራትን ለሚያረጋግጡ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቶ ተሠርቷል ብለዋል፡፡ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ለማስፋፋት በርካታ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በመላው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ34ሺህ በላይ የመዋዕለ ሕፃናት መገንባታቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ከአራት ሚሊየን በላይ ሕፃናት በትምህርት ገበታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። የትምህርት ሚኒስትር ደኤታ አየለች እሸቴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ መንግሥት ለትምህርት ጥራት መሻሻል ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ለዚህም በነባር የትምህርት ፍኖተ ካርታው ላይ የተመላከቱ ችግሮችን በጥናት በመለየት የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲው ለጥራት ቅድሚያ በሚሰጥ መልኩ እንዲሻሻል መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ የቀድሞው ሥርዓተ ትምህርት የነበሩበትን ክፍተቶች በዝርዝር በመለየት አዲስና ሥርዓተ ትምህርት ተቀርጾ ወደ ተግባር መገባቱን ጠቁመው ይህም በዘርፉ ትልቅ ስኬት ተደርጎ እንደሚወሰድ ገልጸዋል። አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተማሪዎች ዘመኑ የሚጠይቀውን ዕውቀትና ክህሎት እንዲጨብጡ ለማስቻል ብቃትን መሠረት ያደረገ ሆኖ መዘጋጀቱንም ነው የገለጹት፡፡ ይህም ተማሪዎች የንድፈ ሃሳብ ዕውቀት ብቻ ሳይሆን ተግባራዊ ክህሎትንም እንዲያዳብሩ ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየታዩበት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፖሊሲና በሥርዓተ ትምህርት ደረጃ የተወሰዱት እነዚህ የለውጥ እርምጃዎች በትምህርት ዘርፉ የታየውን ስብራት ለመጠገንና ብቁ ትውልድ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ጉልህ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በትምህርት ለትውልድ መርሐ-ግብር ማህበረሰቡንና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርትን ከመሠረቱ ለማስተካከል ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። በዚህ ንቅናቄ በሺዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቁመው በርካታ ከደረጃ በታች የነበሩ ትምህርት ቤቶች ደረጃቸው እንዲሻሻል መደረጉን ጠቁመዋል፡፡ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የትምህርት ቤቶችን አካባቢ ከአዋኪ ድርጊቶች ነጻ ማድረግ ማስቻሉን ተከትሎ ለመማር ማስተማር ሂደቱ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ነው ያሉት፡፡ በዚህም ተማሪዎች በትምህርታቸው ላይ ብቻ እንዲያተኩሩና በመልካም ሥነ-ምግባር እንዲታነጹ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይም የተጀመሩ የለውጥ ሥራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል በዕውቀትና በሥነ-ምግባር የበለጸገ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ልማት ላይ ያተኮሩ ዓይኖች እና መበልጸግን የሚያሰላስሉ የልቦና ውቅሮች ውጤት ነው 
Feb 7, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2018(ኢዜአ)፦ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ልማት ላይ ያተኮሩ ዓይኖች፣ መበልጸግን የሚያሰላስሉ የልቦና ውቅሮች እና በጎ መስራትን የሚያስቡ አዕምሮዎች ውጤት መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በገበታ ለትውልድ ውጥን የተገነባው እና በ13 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውን ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት መርቀዋል።   የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት፤ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ለአካባቢው ግርማ ሞገስ ያጎናጸፈና ለክልሉ ሁለንተናዊ ልማት ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ሪዞርቱ ከሆቴል አገልግሎት ባለፈ ትልቅ የታሪክና የቱሪዝም ድልድይ መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡ ሪዞርቱ አዲስ አበባን፣ ለአድዋ ድል ክተት የታወጀበት ወረኢሉን፣ የውጫሌ ውል የተሰናዳበትን ይስማ ንጉስን፣ ማይጨውንና የጥቁር ህዝቦች የድል አድራጊነት ምልክት የሆነውን አደዋን የሚያስተሳስር የቱሪስት ፍሰት መስመር ሆኖ እንደሚያገለግል ገልጸዋል፡፡ በአማራ ክልል ደሴንና ኮምቦልቻን እንዲሁም በአቅራቢያው የሚገኙ ከተሞችን በማገናኘት ወደፊት ለሚመሰረተው ታላቁ የቀጠናው ከተማ ትልቅ ግብዓት ይሆናልም ብለዋል።   አካባቢው በርካታ እድሜ ጠገብ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ታሪካዊ መስህቦች ያሉበት ቢሆንም፣ በመዳረሻ ልማት እጥረት ምክንያት ከቱሪስቶች ርቆ መቆየቱን ነው ያስታወሱት፡፡ ዛሬ የተመረቀው ሪዞርት ይህንን ችግር በዘላቂነት በመቅረፍ የሀገርን ገጽታና የህዝብን ክብር ከፍ የሚያደርጉ ሌሎች መሰል ልማቶችን ለማከናወን አርአያ እንደሚሆንም ገልጸዋል።   ሪዞርቱ በጎ መስራትን የሚያስቡ አዕምሮዎች የጋራ ድል መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።  

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ምክክሩ በአጀንዳዎች ላይ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር ጉልህ ጠቀሜታ አለው
Feb 8, 2026 67
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሴቶችና ወጣቶች በሚያነሷቸው አጀንዳዎች ላይ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለው የአዲስ አበባ ሴቶችና ወጣቶች ማኅበራት አስገነዘቡ። የአዲስ አበባ ሴቶች ማኅበር ፕሬዚዳንት እናትዓለም እንዳለ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክር በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።   የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል የውይይት መድረክ በማካሄድ አለመግባባቶችን በጸና ሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚተካ ሁነኛ መፍትሔ መሆኑን ጠቁመዋል። ማኅበራቸው በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረኮች ላይ የነቃ ተሳትፎ ማድረጉንም አስታውቀዋል። በቀጣይም ለሀገራዊ ምክክሩ በቀረቡ አጀንዳዎች መነሻነት በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ላይ ሴቶችን የተመለከቱ አጀንዳዎችን በመለየት ንቁ ተሳትፎ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።   የአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር ፕሬዚዳንት በረከት ብርቢርሳ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል ወሳኝ ዕድል ነው ብለዋል። በቀጣይም በሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ የነበራቸውን ተሳትፎ በማስቀጠል ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ሀገርን ማዕከል በማድረግ የሴቶችና ወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚያስችሉ መስኮች ላይ በትኩረት እንደሚሠሩም ፕሩዚዳንቶቹ ለኢዜአ ገልጸዋል።
በመዲናዋ የተመዘገቡ የልማት ሥራዎች ለሕብረቱ የመሪዎች ጉባዔ ድምቀት ሆነዋል
Feb 8, 2026 48
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተመዘገቡ አስደማሚ የልማት ሥራዎች ለ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ተደማሪ ድምቀት መሆናቸውን የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለጹ። የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርና ሌሎች መሠረተ ልማቶች ከተማዋን ለነዋሪምቹ ከማድረጋቸው ባለፈ የአፍሪካ መዲናነቷን እያረጋገጡ እንደሚገኙ ነዋሪዎቹ ለኢዜአ ተናግረዋል።   ከነዋሪዎች መካከል ዘሪሁን ግሩም እንዳሉት፤ አዲስ አበባ የአፍሪካ ሕብረትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ ብትሆንም ቀደም ሲል የነበረው የከተማዋ ገጽታ ስሟን የሚመጥን አልነበረም። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ለነዋሪዎቿ ምቹ ከመሆን ባለፈ ለአፍሪካም አርአያ የሚሆኑ ተግባራት መሆናቸውን አስረድተዋል።   ኢትዮጵያ የአፍሪካ እና የመላ ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ቀንዲል መሆኗን የገለጹት እንዳሻው ፍቃዱ፤ በዕድገት እና በልማትም ግንባር ቀደም መሆኗም እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል   የልማት ሥራዎቹ የሀገርን ክብር ከፍ ከማድረጋቸው ባለፈ የዜጎችን ኑሮ የሚቀይሩ የኢኮኖሚ ዕድሎችን እንደሚፈጥሩ የገለጹት ደግሞ አየለ አንጀሎ እና ሙሉቀን ተስፋዬ ናቸው።   39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ከየካቲት 7 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓትን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በብሔራዊ መግባባት የተመሰረተ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ወሳኝ ነው - የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት
Feb 7, 2026 93
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በብሔራዊ መግባባት የተመሰረተ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል የምክክር አውድ ለመፍጠር በወሳኝ የምክክር ምዕራፍ ላይ ይገኛል። የምክክር ሂደቱም ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምና ደኅንነትን በማጽናት ጠንካራ ሀገረ መንግስትና ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየሰራ ነው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዘላቂ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል ወሳኝ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል ግዛቸው አይካ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አካታችና አሰባሳቢ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል የሚስተዋሉ አለመግባባቶችን ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱም በሰለጠነ የጠረጴዛ ላይ የምክክር ሥርዓት የቆዩ ሀገራዊ ቅራዎችን በአዲስ የምክክር ምዕራፍ ዘላቂ እልባት ለመስጠት በድልድይነት የሚያገለግል መሆኑን ተናግረዋል።   ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ሀገረ ለማስተላለፍ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል ምክክርን መከተል ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ ሌላኛው የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል አቶ መስፍን መንግስቱ ናቸው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሰለጠነ ምክክር በማካሄድ ጠንካራ ሀገረ መንግስትን ለመገንባት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ሀገራዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።  
ማህበሩ ምርጫው ሠላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻውን ይወጣል
Feb 7, 2026 96
አምቦ፤ጥር 30/2018(ኢዜአ)፡- የምዕራብ ሸዋ ዞን ወጣቶች ማህበር ምርጫው ሠላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ገለጸ። በምዕራብ ሸዋ ዞን ካሉ ወረዳዎች ለተወጣጡ ወጣቶች በመጪው ጠቅላላ ምርጫና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል። በወቅቱም የምዕራብ ሸዋ ዞን ወጣቶች ማህበር ኃላፊ ወጣት ሂርጳሳ ገላል እንደገለፀው፤ ማህበሩ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የወጣቶች ተሳትፎ ከመምረጥና ከመመረጥ ባለፈ ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየሰራ ነው።   ማህበሩ የሲቪክ ማህበር እንደመሆኑ መጠን ምርጫው ነጻ፣ ፍትሐዊ፣ ሠላማዊና ተዓማኒነትን ያተረፈ እንዲሆንም የድርሻውን ለመወጣት ተዘጋጅቷል ብሏል። ወጣቱ በሕገ መንግስቱ የተሰጠውን መብት በመጠቀምም በመምረጥ፣ በመመረጥ፣ በማስመረጥና የምርጫውን ሰላማዊነት በማስጠበቅ ረገድ የላቀ ድርሻና ኃላፊነት እንዳለበትም አስገንዝቧል። ማህበሩ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና ያገኘ መሆኑን ገልፆ ምርጫው ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም የተለያዩ ስራዎችን በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ነው የተናገረው። የምዕራብ ሸዋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምስጋና ከበደ በበኩላቸው፤ ወጣቱ መጪው ጠቅላላ ምርጫ ከጅምሩ እስከ ማጠናቀቂያው ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊያደርግ እንደሚገባም አመልክተዋል። ከስልጠና ተሳታፊዎቹ መካከል ከወልመራ ወረዳ የመጣችው ወጣት ትእግስት ኦሊ በበኩሏ፤ ስልጠናው በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ላይ የጠራ ግንዛቤ እንድትይዝ ማድረጉን ገልፃለች። በአሁኑ ወቅት በአካባቢው ያለውን የተረጋጋ ሰላም በማስቀጠል ምርጫው በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ በቅንጅት ለመስራት ዝግጅት እያደረግን እንገኛለን ነው ያለችው። በመጪው ግንቦት ወር ላይ የሚካሔደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በቴክኖሎጂ መደገፉ ወጣቱ ያለምንም ተግዳሮት ተሳታፊ እንዲሆን የሚያደርግ ነው ያለው ደግሞ ከኢልፈታ ወረዳ የመጣው የስልጠናው ተሳታፊ ወጣት ቦኒ ወርቅነህ ነው።  
ሰራዊቱ ለሀገሩ ክብርና ለዜጎች ደህንነት ከመቼውም ጊዜ በላይ በጀግንነት መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው- ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ
Feb 7, 2026 95
ሰቆጣ፤ ጥር 30/2018(ኢዜአ)፡- ሰራዊቱ ለሀገሩ ክብርና ለዜጎች ደህንነት ከመቼውም ጊዜ በላይ በጀግንነት መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን በሀገር መከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ ገለጹ። የእዙ አመራሮችና አባላት እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎች የተሳተፉበት የፓናል ውይይት በሰቆጣ ከተማ ተካሂዷል።   በመደረኩ ላይ የተገኙት የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ፤ የኢትዮጵያን ክብርና ሉአላዊነት በአስተማማኝ መልኩ የሚያስከብር ጠንካራ ሰራዊት መገንባቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ሰራዊቱ ለሀገሩ ክብርና ለዜጎች ደህንነት ከመቼውም ጊዜ በላይ በጀግንነት መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የባእዳንን ተልእኮ ለመፈፀም የሚንቀሳቀሱ ባንዳዎችን ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ እንዲሁም ለሰላም አማራጭ ዝግጁ የሆኑትን በመቀበል በተለይም በአማራ ክልል የሰላም ማስከበር ስራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በቀጣይም ከውስጥ ባንዳዎችና ከባእዳን ለሚሞከሩ ማናቸውም የጥፋት እንቅስቃሴዎች የሰራዊቱ ፈጣን ምላሽና የወትሮ ዝግጁነት የተሟላ ነው ብለዋል። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጌትነት እሸቱ፤ የዳሎል ማዕከላዊ እዝ የሀገርን ክብርና ሉዓላዊነት ከማስከበር ባለፈ በክልሉ ሰላም በማረጋገጥ ረገድ እያደረገ ላለው አስተዋጽኦ አመስግነዋል።
በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ጠንካራ ፉክክር ለማድረግ መዘጋጀታቸውን የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ
Feb 7, 2026 147
ደሴ፤ ጥር 30/2018( ኢዜአ)፡- በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ጠንካራ ፉክክር ለማድረግ መዘጋጀታቸውን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ። ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ክንውን የምርጫ ቦርድን ህግና አሰራር በማክበር ለመፎካከር ለእጩዎቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ከወዲሁ ግንዛቤ መፍጠራቸውን ፓርቲዎቹ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ መስጫ እለት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ. ም የሚካሄድ ይሆናል። ለምርጫው ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ፉክክር ቦርዱ ለፓርቲዎች እኩል የመወዳደሪያ እድሎችን በመፍጠር ከእጩዎች ምዝገባ ጀምሮ ዜጎች ድምፃቸውን ለመስጠት የምርጫ ካርድ የሚወስዱበትን ቀልጣፋ አሰራር ዘርግቷል። በዚህም መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎቻቸውን በማስመዝገብ ለውድድሩ የተሟላ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ኢዜአ በደሴ ከተማ ካነጋገራቸው ፓርቲዎች መካከል የወሎ ዴሞክራቲክ ፓርቲ፤ የኢዜማ እና ብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በምርጫው ጠንካራ ፉክክር ለማድረግ ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የወሎ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ዳውድ መሀመድ፤ ፓርቲያቸው ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊነት የድርሻውን ለመወጣት መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን ብቁ የሆኑ እጩዎችን በማስመዝገብ ፓሊሲና ስትራቴጂያቸውን ለህዝብ ለማስተዋወቅ የሚያስችሉ ዝግጅቶች ተደርገዋል ብለዋል። በኢዜማ ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ዳኜ ሰብስቤ፤ የዘንድሮው የምርጫ ሂደት በኢትዮጵያ ጥሩ የዴሞክራሲ መሰረት የሚያሲዝ ታሪካዊ ሆኖ እንዲካሄድ የፓርቲዎች ዝግጁነትና ቀና ትብብር መሆኑን አንስተዋል። በዚሁ መሰረትም ኢዜማ ለምርጫው መሳካት የድርሻውን ለመወጣትና ጠንካራ ተፎካካሪ በመሆን የህዝብ ድምፅ ለማግኘት እየተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲያቸው በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ሊያገኙ የሚችሉ ብቁ የሆኑ እጩዎችን እያስመዘገበ መሆኑን አንስተው ለምርጫው መሳካት በተለይም የፖለቲካ ተዋናዮች ሃላፊነት ወስደን መስራት ይገባናል ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሸናፊ አለማየሁ፤ ከለውጡ በኋላ በተፈጠረው ፍትሃዊና አሳታፊ የፖለቲካ ምኅዳር በመጠቀም ፓርቲዎች ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን መዘጋጀታቸውን አንስተዋል። ከዚህ አንፃር ብልፅግና ፓርቲ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ሂደት ፓርቲያቸው የላቀ ሚናውን ለመወጣት መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በምርጫው ሀገርና ህዝብን በብቃት ማገልገል የሚችሉ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን እጩዎች በማስመዝገብ ለውድድሩ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ግልጽ እና ተዓማኒ ለማድረግ የተሟላ ዝግጅት በማድረግ ወደ ስራ መግባቱን መግለጹ ይታወሳል።  
ኮሚሽኑ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ምክክሩን ስኬታማ የሚያደርጉና በአርዓያነት የሚጠቀሱ ተግባራትን አከናውኗል
Feb 6, 2026 124
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ምክክሩን ስኬታማ የሚያደርጉና በአርዓያነት የሚጠቀሱ መጠነ ሰፊ ተግባራት ማከናወኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ ገለጹ። ቋሚ ኮሚቴው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የሥራ አፈጻጸም እና የቀጣይ ዕቅዶችን ገምግሟል።   የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በወቅቱ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ለዘመናት ስር ሰደው የቆዩ ውስብስብ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ስልጡን የፖለቲካ ባሕል በማስፈለጉ የምክክር ኮሚሽኑ ተቋቁሟል። ኮሚሽኑ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ መጠነ ሰፊ ተግባራት ማከናወኑን ገልጸው የሂደቱ አሳታፊነትና አካታችነት ለሌሎች ሀገራት ጭምር ትልቅ ልምድ ሊሆን የሚችል መሆኑን ገልጸዋል። በሂደቱ ልዩነቶችን በኃይል የመፍታት አባዜ ቀርቶ፣ በምክክርና በሀሳብ የበላይነት ወደሚመራ ስልጡን የፖለቲካ ባህል መግባት መጀመሩ ትልቅ ስኬት መሆኑን ጠቅሰዋል። ኮሚሽኑ በብልሃትና በጥንቃቄ ባከናወናቸው ተግባራት እስካሁን በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብና ለዋናው ጉባኤ የሚሳተፉ ሰዎችን የማስመረጥ ሥራ በስኬት ማከናወኑ ይበል የሚያሰኝ መሆኑንም አንስተዋል። ይህ ተግባር ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል ጠንካራ መሠረት እየጣለ መሆኑን ተናግረዋል። ሕዝቡ በምክክሩ ትልቅ ተስፋ መሰነቁን ጠቅሰው ቀሪ ሥራዎችን ለማሳካት ሁሉም ሚናውን መወጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በትግራይ ክልል የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ማፋጠን እንደሚገባ ጠቅሰው፥ ባለድርሻ አካላትም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ሰብሳቢው ጥሪ አስተላልፈዋል።   የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራው አንደሞ በበኩላቸው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አመርቂ ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። የምክክሩና የአጀንዳው ዋና ባለቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑን ጠቅሰው ሂደቱ የሁሉንም ሕዝብ ተሳትፎ በማረጋገጥ በኩል ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል። ወደ ዋናው የምክክር ጉባኤ ለመግባት አመቻቾችንና አወያዮችን በፍጥነት የማሰልጠን ሥራ በትኩረት ሊከናወን እንደሚገባ አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፥ የኮሚሽኑ የሥራ አፈጻጸም አካታችነትን በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል።   እስካሁን ባለው ሂደት ከ1ሺህ 234 ወረዳዎች አጀንዳዎችን የማሰባሰብና ለዋናው ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ሥራ በስኬት መከናወኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ከ38 የፌዴራል ተቋማት፣ ማኅበራት እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አጀንዳዎች ተሰብስበው የማደራጀት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኮሚሽኑ የሥራ ሂደቱን ለማቀላጠፍ የአሠራር ሥርዓቱን በዲጂታል የታገዘ ማድረግ መቻሉንም ጠቁመዋል። ሀገራዊ አጀንዳዎችን ማጽደቅ፣ እጅግ መሠረታዊ የሚባሉ አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ ማድረግ፣ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ማጠናቀቅ እና ዋናውን ሀገራዊ ጉባኤ ማካሄድ በቀጣይ በትኩረት የሚከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።  
ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ግብዓት የሚሆኑ አጀንዳዎች ማሰባሰብ እና ልየታ ላይ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል
Feb 6, 2026 133
አዲስ አበባ፤ጥር 29/2018 (ኢዜአ)፡-ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ግብዓት የሚሆኑ አጀንዳዎች ማሰባሰብ እና ልየታ ላይ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቃል አቃባይ ጥበቡ ታደሰ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የሃሳብ ልዩነቶችና አለመግባባቶችን በምክክርና በሰለጠነ መንገድ በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡ ይህም ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ከፍተኛ አበርክቶ ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም ኮሚሽኑ ሁሉን አሳታፊና አካታች መርህን በመከተል የሁሉም ድምጽ የተሰማበት ውጤታማ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ማከናወኑን ገልጸዋል። በፌደራል ደረጃ፣በክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከዳያስፖራው ማኀበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ መቻሉን አብራርተዋል። አጀንዳ ልየታ ላይም በተመሳሳይ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው፥ በዋናው ምክክር ላይ የሚሳተፉ ተሳታፊዎችም መለየት መቻሉን አስረድተዋል። እንደ አቶ ጥበቡ ገለጻ፥ የምክክር ኮሚሽኑ እስከ አሁን በመጣበት ሂደትና በፈጠራቸው መድረኮች የምክክሩ ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን በነጻነት መግለጽ የሚችሉበት ምቹ አውድ ተፈጥሯል። የሀሳብ ልዩነቶችንና አለመግባባቶች መንስዔ የሆኑ ጉዳዮች በውይይትና በምክክር በመፍታት የተሻለች ሀገር መገንባት እንደሚቻል ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል።
ፖለቲካ
ምክክሩ በአጀንዳዎች ላይ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር ጉልህ ጠቀሜታ አለው
Feb 8, 2026 67
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሴቶችና ወጣቶች በሚያነሷቸው አጀንዳዎች ላይ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለው የአዲስ አበባ ሴቶችና ወጣቶች ማኅበራት አስገነዘቡ። የአዲስ አበባ ሴቶች ማኅበር ፕሬዚዳንት እናትዓለም እንዳለ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክር በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።   የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል የውይይት መድረክ በማካሄድ አለመግባባቶችን በጸና ሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚተካ ሁነኛ መፍትሔ መሆኑን ጠቁመዋል። ማኅበራቸው በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረኮች ላይ የነቃ ተሳትፎ ማድረጉንም አስታውቀዋል። በቀጣይም ለሀገራዊ ምክክሩ በቀረቡ አጀንዳዎች መነሻነት በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ላይ ሴቶችን የተመለከቱ አጀንዳዎችን በመለየት ንቁ ተሳትፎ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።   የአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር ፕሬዚዳንት በረከት ብርቢርሳ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል ወሳኝ ዕድል ነው ብለዋል። በቀጣይም በሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ የነበራቸውን ተሳትፎ በማስቀጠል ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ሀገርን ማዕከል በማድረግ የሴቶችና ወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚያስችሉ መስኮች ላይ በትኩረት እንደሚሠሩም ፕሩዚዳንቶቹ ለኢዜአ ገልጸዋል።
በመዲናዋ የተመዘገቡ የልማት ሥራዎች ለሕብረቱ የመሪዎች ጉባዔ ድምቀት ሆነዋል
Feb 8, 2026 48
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተመዘገቡ አስደማሚ የልማት ሥራዎች ለ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ተደማሪ ድምቀት መሆናቸውን የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለጹ። የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርና ሌሎች መሠረተ ልማቶች ከተማዋን ለነዋሪምቹ ከማድረጋቸው ባለፈ የአፍሪካ መዲናነቷን እያረጋገጡ እንደሚገኙ ነዋሪዎቹ ለኢዜአ ተናግረዋል።   ከነዋሪዎች መካከል ዘሪሁን ግሩም እንዳሉት፤ አዲስ አበባ የአፍሪካ ሕብረትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ ብትሆንም ቀደም ሲል የነበረው የከተማዋ ገጽታ ስሟን የሚመጥን አልነበረም። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ለነዋሪዎቿ ምቹ ከመሆን ባለፈ ለአፍሪካም አርአያ የሚሆኑ ተግባራት መሆናቸውን አስረድተዋል።   ኢትዮጵያ የአፍሪካ እና የመላ ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ቀንዲል መሆኗን የገለጹት እንዳሻው ፍቃዱ፤ በዕድገት እና በልማትም ግንባር ቀደም መሆኗም እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል   የልማት ሥራዎቹ የሀገርን ክብር ከፍ ከማድረጋቸው ባለፈ የዜጎችን ኑሮ የሚቀይሩ የኢኮኖሚ ዕድሎችን እንደሚፈጥሩ የገለጹት ደግሞ አየለ አንጀሎ እና ሙሉቀን ተስፋዬ ናቸው።   39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ከየካቲት 7 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓትን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በብሔራዊ መግባባት የተመሰረተ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ወሳኝ ነው - የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት
Feb 7, 2026 93
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በብሔራዊ መግባባት የተመሰረተ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል የምክክር አውድ ለመፍጠር በወሳኝ የምክክር ምዕራፍ ላይ ይገኛል። የምክክር ሂደቱም ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምና ደኅንነትን በማጽናት ጠንካራ ሀገረ መንግስትና ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየሰራ ነው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዘላቂ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል ወሳኝ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል ግዛቸው አይካ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አካታችና አሰባሳቢ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል የሚስተዋሉ አለመግባባቶችን ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱም በሰለጠነ የጠረጴዛ ላይ የምክክር ሥርዓት የቆዩ ሀገራዊ ቅራዎችን በአዲስ የምክክር ምዕራፍ ዘላቂ እልባት ለመስጠት በድልድይነት የሚያገለግል መሆኑን ተናግረዋል።   ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ሀገረ ለማስተላለፍ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል ምክክርን መከተል ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ ሌላኛው የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል አቶ መስፍን መንግስቱ ናቸው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሰለጠነ ምክክር በማካሄድ ጠንካራ ሀገረ መንግስትን ለመገንባት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ሀገራዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።  
ማህበሩ ምርጫው ሠላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻውን ይወጣል
Feb 7, 2026 96
አምቦ፤ጥር 30/2018(ኢዜአ)፡- የምዕራብ ሸዋ ዞን ወጣቶች ማህበር ምርጫው ሠላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ገለጸ። በምዕራብ ሸዋ ዞን ካሉ ወረዳዎች ለተወጣጡ ወጣቶች በመጪው ጠቅላላ ምርጫና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል። በወቅቱም የምዕራብ ሸዋ ዞን ወጣቶች ማህበር ኃላፊ ወጣት ሂርጳሳ ገላል እንደገለፀው፤ ማህበሩ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የወጣቶች ተሳትፎ ከመምረጥና ከመመረጥ ባለፈ ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየሰራ ነው።   ማህበሩ የሲቪክ ማህበር እንደመሆኑ መጠን ምርጫው ነጻ፣ ፍትሐዊ፣ ሠላማዊና ተዓማኒነትን ያተረፈ እንዲሆንም የድርሻውን ለመወጣት ተዘጋጅቷል ብሏል። ወጣቱ በሕገ መንግስቱ የተሰጠውን መብት በመጠቀምም በመምረጥ፣ በመመረጥ፣ በማስመረጥና የምርጫውን ሰላማዊነት በማስጠበቅ ረገድ የላቀ ድርሻና ኃላፊነት እንዳለበትም አስገንዝቧል። ማህበሩ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና ያገኘ መሆኑን ገልፆ ምርጫው ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም የተለያዩ ስራዎችን በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ነው የተናገረው። የምዕራብ ሸዋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምስጋና ከበደ በበኩላቸው፤ ወጣቱ መጪው ጠቅላላ ምርጫ ከጅምሩ እስከ ማጠናቀቂያው ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊያደርግ እንደሚገባም አመልክተዋል። ከስልጠና ተሳታፊዎቹ መካከል ከወልመራ ወረዳ የመጣችው ወጣት ትእግስት ኦሊ በበኩሏ፤ ስልጠናው በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ላይ የጠራ ግንዛቤ እንድትይዝ ማድረጉን ገልፃለች። በአሁኑ ወቅት በአካባቢው ያለውን የተረጋጋ ሰላም በማስቀጠል ምርጫው በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ በቅንጅት ለመስራት ዝግጅት እያደረግን እንገኛለን ነው ያለችው። በመጪው ግንቦት ወር ላይ የሚካሔደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በቴክኖሎጂ መደገፉ ወጣቱ ያለምንም ተግዳሮት ተሳታፊ እንዲሆን የሚያደርግ ነው ያለው ደግሞ ከኢልፈታ ወረዳ የመጣው የስልጠናው ተሳታፊ ወጣት ቦኒ ወርቅነህ ነው።  
ሰራዊቱ ለሀገሩ ክብርና ለዜጎች ደህንነት ከመቼውም ጊዜ በላይ በጀግንነት መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው- ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ
Feb 7, 2026 95
ሰቆጣ፤ ጥር 30/2018(ኢዜአ)፡- ሰራዊቱ ለሀገሩ ክብርና ለዜጎች ደህንነት ከመቼውም ጊዜ በላይ በጀግንነት መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን በሀገር መከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ ገለጹ። የእዙ አመራሮችና አባላት እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎች የተሳተፉበት የፓናል ውይይት በሰቆጣ ከተማ ተካሂዷል።   በመደረኩ ላይ የተገኙት የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ፤ የኢትዮጵያን ክብርና ሉአላዊነት በአስተማማኝ መልኩ የሚያስከብር ጠንካራ ሰራዊት መገንባቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ሰራዊቱ ለሀገሩ ክብርና ለዜጎች ደህንነት ከመቼውም ጊዜ በላይ በጀግንነት መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የባእዳንን ተልእኮ ለመፈፀም የሚንቀሳቀሱ ባንዳዎችን ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ እንዲሁም ለሰላም አማራጭ ዝግጁ የሆኑትን በመቀበል በተለይም በአማራ ክልል የሰላም ማስከበር ስራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በቀጣይም ከውስጥ ባንዳዎችና ከባእዳን ለሚሞከሩ ማናቸውም የጥፋት እንቅስቃሴዎች የሰራዊቱ ፈጣን ምላሽና የወትሮ ዝግጁነት የተሟላ ነው ብለዋል። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጌትነት እሸቱ፤ የዳሎል ማዕከላዊ እዝ የሀገርን ክብርና ሉዓላዊነት ከማስከበር ባለፈ በክልሉ ሰላም በማረጋገጥ ረገድ እያደረገ ላለው አስተዋጽኦ አመስግነዋል።
በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ጠንካራ ፉክክር ለማድረግ መዘጋጀታቸውን የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ
Feb 7, 2026 147
ደሴ፤ ጥር 30/2018( ኢዜአ)፡- በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ጠንካራ ፉክክር ለማድረግ መዘጋጀታቸውን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ። ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ክንውን የምርጫ ቦርድን ህግና አሰራር በማክበር ለመፎካከር ለእጩዎቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ከወዲሁ ግንዛቤ መፍጠራቸውን ፓርቲዎቹ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ መስጫ እለት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ. ም የሚካሄድ ይሆናል። ለምርጫው ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ፉክክር ቦርዱ ለፓርቲዎች እኩል የመወዳደሪያ እድሎችን በመፍጠር ከእጩዎች ምዝገባ ጀምሮ ዜጎች ድምፃቸውን ለመስጠት የምርጫ ካርድ የሚወስዱበትን ቀልጣፋ አሰራር ዘርግቷል። በዚህም መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎቻቸውን በማስመዝገብ ለውድድሩ የተሟላ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ኢዜአ በደሴ ከተማ ካነጋገራቸው ፓርቲዎች መካከል የወሎ ዴሞክራቲክ ፓርቲ፤ የኢዜማ እና ብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በምርጫው ጠንካራ ፉክክር ለማድረግ ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የወሎ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ዳውድ መሀመድ፤ ፓርቲያቸው ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊነት የድርሻውን ለመወጣት መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን ብቁ የሆኑ እጩዎችን በማስመዝገብ ፓሊሲና ስትራቴጂያቸውን ለህዝብ ለማስተዋወቅ የሚያስችሉ ዝግጅቶች ተደርገዋል ብለዋል። በኢዜማ ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ዳኜ ሰብስቤ፤ የዘንድሮው የምርጫ ሂደት በኢትዮጵያ ጥሩ የዴሞክራሲ መሰረት የሚያሲዝ ታሪካዊ ሆኖ እንዲካሄድ የፓርቲዎች ዝግጁነትና ቀና ትብብር መሆኑን አንስተዋል። በዚሁ መሰረትም ኢዜማ ለምርጫው መሳካት የድርሻውን ለመወጣትና ጠንካራ ተፎካካሪ በመሆን የህዝብ ድምፅ ለማግኘት እየተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲያቸው በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ሊያገኙ የሚችሉ ብቁ የሆኑ እጩዎችን እያስመዘገበ መሆኑን አንስተው ለምርጫው መሳካት በተለይም የፖለቲካ ተዋናዮች ሃላፊነት ወስደን መስራት ይገባናል ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሸናፊ አለማየሁ፤ ከለውጡ በኋላ በተፈጠረው ፍትሃዊና አሳታፊ የፖለቲካ ምኅዳር በመጠቀም ፓርቲዎች ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን መዘጋጀታቸውን አንስተዋል። ከዚህ አንፃር ብልፅግና ፓርቲ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ሂደት ፓርቲያቸው የላቀ ሚናውን ለመወጣት መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በምርጫው ሀገርና ህዝብን በብቃት ማገልገል የሚችሉ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን እጩዎች በማስመዝገብ ለውድድሩ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ግልጽ እና ተዓማኒ ለማድረግ የተሟላ ዝግጅት በማድረግ ወደ ስራ መግባቱን መግለጹ ይታወሳል።  
ኮሚሽኑ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ምክክሩን ስኬታማ የሚያደርጉና በአርዓያነት የሚጠቀሱ ተግባራትን አከናውኗል
Feb 6, 2026 124
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ምክክሩን ስኬታማ የሚያደርጉና በአርዓያነት የሚጠቀሱ መጠነ ሰፊ ተግባራት ማከናወኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ ገለጹ። ቋሚ ኮሚቴው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የሥራ አፈጻጸም እና የቀጣይ ዕቅዶችን ገምግሟል።   የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በወቅቱ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ለዘመናት ስር ሰደው የቆዩ ውስብስብ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ስልጡን የፖለቲካ ባሕል በማስፈለጉ የምክክር ኮሚሽኑ ተቋቁሟል። ኮሚሽኑ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ መጠነ ሰፊ ተግባራት ማከናወኑን ገልጸው የሂደቱ አሳታፊነትና አካታችነት ለሌሎች ሀገራት ጭምር ትልቅ ልምድ ሊሆን የሚችል መሆኑን ገልጸዋል። በሂደቱ ልዩነቶችን በኃይል የመፍታት አባዜ ቀርቶ፣ በምክክርና በሀሳብ የበላይነት ወደሚመራ ስልጡን የፖለቲካ ባህል መግባት መጀመሩ ትልቅ ስኬት መሆኑን ጠቅሰዋል። ኮሚሽኑ በብልሃትና በጥንቃቄ ባከናወናቸው ተግባራት እስካሁን በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብና ለዋናው ጉባኤ የሚሳተፉ ሰዎችን የማስመረጥ ሥራ በስኬት ማከናወኑ ይበል የሚያሰኝ መሆኑንም አንስተዋል። ይህ ተግባር ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል ጠንካራ መሠረት እየጣለ መሆኑን ተናግረዋል። ሕዝቡ በምክክሩ ትልቅ ተስፋ መሰነቁን ጠቅሰው ቀሪ ሥራዎችን ለማሳካት ሁሉም ሚናውን መወጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በትግራይ ክልል የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ማፋጠን እንደሚገባ ጠቅሰው፥ ባለድርሻ አካላትም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ሰብሳቢው ጥሪ አስተላልፈዋል።   የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራው አንደሞ በበኩላቸው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አመርቂ ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። የምክክሩና የአጀንዳው ዋና ባለቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑን ጠቅሰው ሂደቱ የሁሉንም ሕዝብ ተሳትፎ በማረጋገጥ በኩል ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል። ወደ ዋናው የምክክር ጉባኤ ለመግባት አመቻቾችንና አወያዮችን በፍጥነት የማሰልጠን ሥራ በትኩረት ሊከናወን እንደሚገባ አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፥ የኮሚሽኑ የሥራ አፈጻጸም አካታችነትን በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል።   እስካሁን ባለው ሂደት ከ1ሺህ 234 ወረዳዎች አጀንዳዎችን የማሰባሰብና ለዋናው ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ሥራ በስኬት መከናወኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ከ38 የፌዴራል ተቋማት፣ ማኅበራት እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አጀንዳዎች ተሰብስበው የማደራጀት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኮሚሽኑ የሥራ ሂደቱን ለማቀላጠፍ የአሠራር ሥርዓቱን በዲጂታል የታገዘ ማድረግ መቻሉንም ጠቁመዋል። ሀገራዊ አጀንዳዎችን ማጽደቅ፣ እጅግ መሠረታዊ የሚባሉ አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ ማድረግ፣ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ማጠናቀቅ እና ዋናውን ሀገራዊ ጉባኤ ማካሄድ በቀጣይ በትኩረት የሚከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።  
ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ግብዓት የሚሆኑ አጀንዳዎች ማሰባሰብ እና ልየታ ላይ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል
Feb 6, 2026 133
አዲስ አበባ፤ጥር 29/2018 (ኢዜአ)፡-ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ግብዓት የሚሆኑ አጀንዳዎች ማሰባሰብ እና ልየታ ላይ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቃል አቃባይ ጥበቡ ታደሰ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የሃሳብ ልዩነቶችና አለመግባባቶችን በምክክርና በሰለጠነ መንገድ በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡ ይህም ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ከፍተኛ አበርክቶ ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም ኮሚሽኑ ሁሉን አሳታፊና አካታች መርህን በመከተል የሁሉም ድምጽ የተሰማበት ውጤታማ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ማከናወኑን ገልጸዋል። በፌደራል ደረጃ፣በክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከዳያስፖራው ማኀበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ መቻሉን አብራርተዋል። አጀንዳ ልየታ ላይም በተመሳሳይ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው፥ በዋናው ምክክር ላይ የሚሳተፉ ተሳታፊዎችም መለየት መቻሉን አስረድተዋል። እንደ አቶ ጥበቡ ገለጻ፥ የምክክር ኮሚሽኑ እስከ አሁን በመጣበት ሂደትና በፈጠራቸው መድረኮች የምክክሩ ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን በነጻነት መግለጽ የሚችሉበት ምቹ አውድ ተፈጥሯል። የሀሳብ ልዩነቶችንና አለመግባባቶች መንስዔ የሆኑ ጉዳዮች በውይይትና በምክክር በመፍታት የተሻለች ሀገር መገንባት እንደሚቻል ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል።
ማህበራዊ
ከመሬት ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት የካዳርስተር ምዝገባ ዲጂታላይዝድ እየተደረገ ነው
Feb 8, 2026 32
ደብረ ብርሃን፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፡- ከመሬት ጋር ተያይዞ የሚነሱ የመልካም አሥተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የካዳርስተር ምዝገባ ዲጂታላይዝድ እየተደረገ መሆኑን የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር መሬት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ እታለማሁ ይምታቱ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በከተማዋ የመሬት መረጃዎችን በማዘመን አገልግሎት አሰጣጡን ዲጂታላይዝ እየተደረገ ነው ብለዋል። መሬትን በካዳስተር ሥርዓት መመዝገብ ገቢን ከማሳደግ ባለፈ ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል የጎላ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በያዝነው የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ከ7 ሺህ ለሚልቁ ባለይዞታዎችን ሕጋዊነት የማረጋገጥ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰዋል። ይዞታቸው የተረጋገጠ ከ2 ሺህ 800 በላይ መሬቶችን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ማስገባት መቻሉንም ጠቁመዋል።   በከተማዋ የጠባሴ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ፈለቁ ጌታነህ እና ጌታነህ ሸዋፈራ እንዳሉት፤ ዘመናዊ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ሕገ-ወጥነትን በመከላከል ፍትሐዊ አገልግሎት ማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
የገጠር ኮሪደር የአኗኗር ዘይቤ ፈጥሯል
Feb 8, 2026 36
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፡- የገጠር ኮሪደር ዘመናዊ የቤት ባለቤት በማድረግ ምቹ የአኗኗር ዘይቤ እንደፈጠረላቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የምዕራብ ሸዋ ዞን አርሶ አደሮች ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በበጎ ፈቃድ መርሐ-ግብር ባለሃብቶችን በማስተባበር በምዕራብ ሸዋ ዞን ያስገነባቸውን ዘመናዊ ቤቶች ገንብቶ ለአርሶ አደሮች አስረክቧል።   የመኖሪያ ቤቶቹ መንግሥት የአርሶና አርብቶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ የተገነቡ ናቸው። የፀሐይና ባዮ ጋዝ የኃይል አማራጭ፣ ምቹ የእንስሳት በረት እንዲሁም አንድ የመኖሪያ ቤት ሊያሟላቸው የሚገቡ የቤት ቁሳቁስና አገልግሎቶችን ያሟሉም ናቸው።   የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ አርሶ አደሮችም፤ የገጠር ኮሪደር ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶቹ የኑሮ ዘይቤያቸውን በመቀየር ምቹ የመኖሪያ ከባቢ እንደፈጠሩላቸው ለኢዜአ ገልጸዋል።   በዞኑ የደንዲ ወረዳ ነዋሪ ሌንሴ ደበሌ፤ ከዚህ ቀደም የነበራቸው ደሳሳ ጎጆ በየዓመቱ ክረምት በመጣ ቁጥር በዝናብ ምክንያት ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰዋል። በሞት ካጧቸው ባለቤታቸው ካፈሯቸው አምስት ልጆቻቸው ጋር በደሳሳ ጎጆዋ ውስጥ በዝናብና በብርድ ጎስቋላ ኑሮን ለመምራት ተገደው መቆየታቸውንም ያወሳሉ። በተሻለ ጥራት ተገንብቶ የተሰጣቸው የመኖሪያ ቤትም ያሳለፉትን አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ በመቀየር ምቹና እፎይታን የቸረ ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ የሚመሩበትን ዕድል እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።   በምዕራብ ሸዋ ዞን የኤጀርሳ ለፎ ወረዳ ነዋሪ ዳማሳ ሆርዶፋ በበኩላቸው ጧሪና ደጋፊ እንደሌላቸው በመጥቀስ፤ መኖሪያ ቤታቸው አርጅቶ ከላያቸው ላይ ሊፈርስ ተቃርቦ እንደነበር ገልጸዋል። የተበረከተላቸው ሁሉም ነገር የተሟላለት ዘመናዊ የመኖሪያ ቤትም፤ የማምሻ ዕድሜያቸውን ከጨለማ ወደ ብርሃን የለወጠ ምሥጋና የሚቸረው አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው በደስታ ተናግረዋል።   የተበረከተላቸው የመኖሪያ ቤት ንጹህና ሁሉንም መሠረተ ልማቶች ያሟሉና ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤን ያጎናጸፉ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ በዞኑ ደንዲ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አርፋሴ ፊጣ ናቸው።   በዞኑ ኤጀርሳ ለፎ ወረዳ ነዋሪዋ ብርቄ ፉፋ በበኩላቸው፤ የገጠር ኮሪደር ጎስቋላ ኑሯቸውን በመቀየር ምቹ ሁኔታ የአኗኗር ዘይቤን የሚመሩበት አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።   የአርሶ አደሩን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶችን ገንብተው ላበረከቱላቸው ተቋማትና ግለሰቦች ምሥጋና አቅርበዋል።
በኦሮሚያ ክልል የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Feb 8, 2026 40
ሐረር፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ከጊዜ ከወደ ጊዜ ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አስታውቋል። ቢሮው የበጀት ዓመቱን ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።   የቢሮው ምክትል ኃላፊ መሐመድናስር አባጀማል (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ባለፉት ስድስት ወራት በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት መከናወናቸውን አረጋግጠዋል። ከነዚህም መካከል የአረንጓዴ ዐሻራ፣ የዐቅመ ደካሞች ቤት ግንባታና እድሳት፣ የትምህርት መርጃ ቁሳቁስና የማጠናከርያ ትምህርት፣ የመንገድ ግንባታ፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ግንባታና የመማሪያ ክፍሎች እድሳት፣ ነጻ የጤና ሕክምና፣ ሞዴል ፋርማሲና ሌሎች ተግባራትን ጨምሮ 72 ዓይነት ሥራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል። በተግባራቱም የክልሉ ነዋሪ ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፤ በሕዝብ ዘንድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠሉን አስገንዝበዋል።   መንግሥት ለማኅበረሰቡ ልማት ምቹ ሁኔታን ከፈጠረ፤ ሕዝቡ ማሳደግና መጠቀም እንደሚችል ተምሳሌታዊ ሥራን አሳይቷል ሲሉም አስረድተዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ከመቅረፍ ባለፈ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የመደጋገፍና የአብሮነት ባህልን እያሳደገ ነው ብለዋል።
በከተማዋ የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ ለማስተናገድ በቂ ዝግጅት ተደርጓል-ቢሮው
Feb 7, 2026 73
ሆሳዕና ፤ ጥር 30/2018(ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ የሚካሄደውን 6ተኛውን ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ ለማስተናገድ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የቢሮው ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንሱን ለማስተናገድ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ ስድስተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በመጪዎቹ የካቲት 4 እና 5/2018 ዓ/ም ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሆሳዕና ከተማ ሊካሄድ ቀነ ቀጠሮ ተይዞለታል ብለዋል። በሀገር አቀፉ የሰላም ኮንፈረንስ ላይም ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የሚመጡ በርካታ እንግዶች እንደሚሳተፉ ጠቁመው ሲከናወን የቆየው ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ በአደባባይ በሚከበረው በዓል ላይም ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎችን ጨምሮ ከ45 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል። የሰላም ኮንፈረንሱ በሲምፖዚየምና በአደባባይ እንደሚዘከር ያነሱት ኃላፊው በህዝቦች መካከል ዘላቂ ሰላምንና አብሮነትን ለማጠናከር የሚረዱ ባህላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች በሲምፖዚየሙ ላይ ተሞክሮ ቀርቦባቸው ውይይት እንደሚደረግም አስረድተዋል፡፡
ኢኮኖሚ
የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋን የቱሪዝም መስህብነት አሳድገዋል
Feb 8, 2026 59
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):-በመዲናዋ የተገነቡ የኮሪደር ልማትና ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋን የቱሪዝም መስህብነት ማሳደጋቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ቱሪዝም ኮሚሽን ገለጸ። "ብስከሌትን በአዲስ" በሚል መሪ ሃሳብ የብስክሌት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ እየተካሄደ ይገኛል። የአዲስ አበባ ከተማ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ቢንያም ታዬ ፤ የቱሪዝም ዘርፍ የዓለም ዋነኛ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ኢንዱስትሪ መሆኑን ገልጸዋል።   ዘርፉ ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል ፈጠራ፣ ለውጭ ንግድ፣ ለኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እና ጥቅል ሀገራዊ ምርት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሀገሪቱን ፈርጀ-ብዙ የቱሪዝም ሃብቶች በስፋት በማልማት ተገቢውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲያስገኝ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። በአዲስ አበባ በኮሪደር ልማትና ወንዝ ዳርቻ የተገነቡ መሰረተ ልማቶች የዚሁ አካል መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይህም የከተማውን ገጽታ የቀየሩና የቱሪዝም መዳረሻዎችን ያሳደጉ ናቸው ብለዋል። የብስክሌት ፌስቲቫሉ በየወሩ የሚከናወን መሆኑን አንስተው ዓለማውም ከተማዋ ያሏት መዳረሻዎችን ለማስተዋወቅና ግንዛቤ ለመፍጠር ነው ብለዋል።   በከተማዋ ኮሪደር ልማትና በወንዝ ዳርቻ የተገነቡ ውብና ሳቢ የሆኑ የቱሪዝም መዳረሻዎች ብስክሌትን እንደ አማራጭ የትራንስፖርት መገልገያነት ተጠቅመው መጎብኘት እንደሚቻል ለማስገንዘብ እንደሆነም አመላክተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አስመሮም ብርሃኔ በበኩላቸው፤ በከተማዋ ሞተር አልባ ትራንስፖርት ለማስፋፋት እየተከናወኑ ከሚገኙ ስራዎች መካከል የብስክሌት ትራንስፖርት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አካባቢ ተፈጥሯዊ ፣ ውብና ሳቢ ገጽታውን ጠብቆ እንዲቆይ ትልቅ አበርክቶ ያለው ነው ብለዋል።
ለሌማት ትሩፋት በተሰጠው ትኩረት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል
Feb 8, 2026 44
ሐረር፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል ለሌማት ትሩፋት በተሰጠው ትኩረት አበረታች ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉ ተገልጿል። የሐረሪ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በሶፊ ወረዳ በርቃ ቀበሌ እየተከናወኑ የሚገኙ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን ተመልክተዋል። የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሔኖክ ሙሉነህ በዚሁ ወቅት፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ የተደረገው የሌማት ትሩፋት በሐረሪ ክልል ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ በወተት፣ እንቁላል፣ በዶሮና ማር ምርት በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉንም አስታውቀዋል። በተለይ የላሞችን ዝርያ በማሻሻል የወተት ምርታማነትን ማሻሻልን ጨምሮ የሥጋ እና ማር ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ ለሌማት ትሩፋት ትኩረት በመስጠት በተሠራው ሥራ የተመዘገበው ውጤት በቤተሰብ ብሎም በሀገር ደረጃ በምግብ ራስን ለመቻል ለሚደረገው ጥረት መሠረት መሆኑን አመላክተዋል።   በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የማር እና ዶሮ መንደር መመስረታቸውን ገልጸው፥ በተጨማሪም የወተት መንደር ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና እነዚህ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።  
በነቀምቴ ከተማ በጎጆ ኢንዱስትሪ ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች ውጤታማ እየሆኑ ነው
Feb 8, 2026 71
ነቀምቴ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):- በምስራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ በጎጆ ኢንዱስትሪ ዘርፍ በማህበር ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ገለጹ። ወጣቶቹ በተሰማሩባቸው የስራ መስኮች ውጤታማ በመሆናቸው ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውን ለኢዜአ ገልጸዋል። በከተማዋ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ለጥቅም በማዋል ስራ ላይ የተሰማራው የአመዩ እና ፍንታዬ ማህበር ሰብሳቢ ወጣት አመዩ ደረጄ በተደራጁ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግሯል።   ማህበሩ ከመንግስት ባገኘው 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ብድር ጥቅም ላይ የዋሉ ፕላስቲኮችን መልሶ በማምረት ለተለያዩ አገልግሎቶች ምርቶችን ለገበያ በማቅረብ ላይ ይገኛል ብሏል። ወጣት አመዩ አክሎም ወጣቶች ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም ማምረት እንዲችሉ መንግስት የሚያመቻቸውን የብድር፣ የመስሪያ ቦታ እንዲሁም ስልጠናና ድጋፍ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አመልክቷል። ማህበራቸውም በዚህ አመት በመደራጀትና ጠንክሮ በመስራት ባስመዘገበው ውጤት ለሌሎች 14 ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁሟል። የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል ወጣት ደራርቱ ገቢሳ በአሁኑ ጊዜ ባገኘቸው የስራ እድል በወር ከ6ሺህ 500 ብር በላይ በማግኘት እየሰራች መሆኗን ገልፃለች። ወደፊትም በሚደረጉ ድጋፎች እና በምታገኘው የስራ ልምድ ራሷን ችላ ለመስራት ማቀዷን ገልፃለች።   ሌላው ሰኚ፣ አዱኛ፣ ኩለኒ እና ጓደኞቻቸው የሽርክና ማህበር ምክትል ሰብሳቢ ወጣት ሰኚ ጋዲሳ አስተዳደሩ ባመቻቸላቸው የመስሪያ ቦታና 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የብድር አቅርቦት በእንጨት ስራ ላይ ተሰማርተው እየሰሩ መሆኑን ገልጿል። በማህበሩ ስር ለአስር ወጣቶች የስራ እድል መከፈቱን አንስቶ ወደ ፊት ስራውን በማስፋት በርካታ ወጣቶችን በስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ተግተን እንሰራለን ነው ያለው። የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር የስራ እድል ፈጠራ እና ክህሎት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ብርሃኑ አሰፋ በከተማዋ ወጣቶችን በማደራጀት ወደ ስራ ለማስገባት በተያዘው እቅድ ውጤታማ የሆኑ ስራዎች እየተመዘገቡ ይገኛሉ ብለዋል።   በተያዘው በጀት አመትም 79 ማህበራትን በማደራጀትና 121 ሚሊዮን ብር በማበደር በተለያዩ ስራዎች ላይ ማሰማራት መቻሉን ገልጸዋል። ወጣቶች አዳዲስ የስራ ሀሳቦችን በማመንጨትና ተደራጅተው በመስራት ለከተማዋ እና አካባቢው ነዋሪዎች ምርቶቻቸውን እያቀረቡ ነው ብለዋል። በከተማዋ ከሚገኙ የጎጆ ኢንዱስትሪ ስራዎችም የሚስማር ማምረቻ፣ የልብስ ስፌት፣ የእንጨት መሰንጠቂያ፣ የብሎኬት እና ቴራዞ ማምረቻዎችና ሌሎች እንደሚገኙ ተናግረዋል። አቶ ብርሃኑ አክለውም በስራው ወጣቶችን ውጤታማ ከማድረግም ባለፈ የስራ ባህላቸውን በመቀየር በቀጣይ ለተሻለ ውጤት ማብቃት ትልቁ ዓላማችን ነው ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩም ለወጣቶቹ የድጋፍ እና ክትትል ተግባራትን የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።
መንግስት የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየመለሰ የልማቱ ተጠቃሚ እያደረገን ነው - ነዋሪዎች
Feb 8, 2026 54
ሀዋሳ ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):-መንግስት የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየመለሰ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን በሲዳማና ኦሮሚያ ክልል ገጠራማ አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች ገለጹ። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በሲዳማና ኦሮሚያ ክልል የገጠር ቀበሌዎች የተከላቸውን የጸሃይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ከሰሞኑ አስመርቋል። ነዋሪዎቹ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የለውጡ መንግስት የመሰረተ ልማት ጥያቄዎቻችንን ደረጃ በደረጃ እየመለሰ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ አድርጎናል ብለዋል። ከሰሞኑ በአካባቢያቸው የተመረቀው የጸሃይ ሃይል ከጨለማ ወደ ብርሃን እንዳሸጋገራቸውና ሰፊ የስራ እድል ይዞ እንደመጣም ተናግረዋል። በሲዳማ ክልል ሎካ አባያ ወረዳ የመሬራ ከተማ ነዋሪው አቶ አሰፋ ሆቶራ መንግስት የዜጎችን ጥያቄ ደረጃ በደረጃ ለመፍታት የሚያደርገው ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል። የትምህርት፣ የጤናና የመንገድ መሰረተ ልማቶች ስለተሟሉላቸው አስፈላጊውን አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ገልጸዋል። አካባቢያቸው ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ርቀት ላይ የሚገኝ በመሆኑ የረዥም ጊዜ የመብራት ጥያቄያቸው ሳይፈታ መቆየቱን አስታውሰው፤ የጸሃይ ሃይልን በመጠቀም በቅርቡ የኤሌክትሪክ መስመር እንደተዘረጋላቸው ተናግረዋል። ይህም የለውጡ መንግስት ለዜጎች የመሰረተ ልማት ጥያቄ አማራጭ መፍትሄ ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል። የዚሁ ከተማ ነዋሪው አቶ ረጋሳ ቡሪሳ በበኩላቸው መንግስት ከገጠር እስከ ከተማ የህብረተሰቡን ጥያቄ ለመመለስ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአካባቢያቸው በተዘረጉ መሰረተ ልማቶች ተጠቅመው ህይወታቸውን በሚቀይሩ ኢኮኖሚያዊ ተግባራት ላይ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። የለውጡ መንግስት አማራጭ የልማት አውታሮችን በመዘርጋት ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት አድንቀው ለአካባቢያቸው ለውጥ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። ለበርካታ ዓመታት የኤሌክትረክ ተጠቃሚ ባለመሆናቸው በማገዶ ሲያበስሉ ጭስ እንደሚጎዳቸው የተናገሩት ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ አርሲ ዞን የነንሰቦ ጨቤ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ ቢርቂሳ መሃመድ ናቸው። የነንሰቦ የጸሃይ ሃይል ማመንጫን ተከትሎ የተዘረጋው መስመር ብርሃን ከመስጠት ባሻገር ለምግብ ማብሰያነትና የተለያዩ ማሽነሪዎችን ለማንቀሳቀስ እያገዘ በመሆኑ መንግስትን አመስግነዋል። የአካባቢው ህዝብ ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየተመለሰ መሆኑን ጠቅሰው የውሃ፣ ጤናና ትምህርት መሰረተ ልማቶችን ለአብነት አንስተዋል። ሌላኛው የነንሰቦ ወረዳ ነዋሪ አቶ መሃመድሁሴን ከድር በበኩላቸው አካባቢው ከፍተኛ የቡና ምርት እንዲሁም ስንዴ እና ገብስ በብዛት የሚመረትበት መሆኑን ተናግረዋል። ምርታማነትን የሚጨምሩ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀሙ በመንግስት በኩል ድጋፍ እየተደረገላቸው በመሆኑ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። የረዥም ጊዜ የኤሌክትሪክ ሃይል ጥያቄ በአማራጭ ኢነርጂ ምላሽ በማግኘቱ መደሰታቸውን ገልጸው አካባቢውን ለመለወጥ እንደሚሰሩም አስታውቀዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጅነር ሱልጣን ወሊ (ደ/ር) መንግስት ታዳሽ የኢነርጂ ሃይልን በመጠቀም ፍትሃዊ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለዜጎች ለማድረስ እየሰራ ነው ብለዋል። በመጪዎቹ ሁለት አመታትም ከ130ሺህ በላይ የቤተሰብ አባላትን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ከ100 በላይ የጸሃይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እንደሚበቁ ተናግረዋል። 750ሺህ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉና በጸሃይ ሃይል የሚሰሩ የቤተሰብ ሻማዎች እንደሚሰራጩና የጤናና የትምህርት ተቋማትን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራትም እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ከ27 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ተደርገዋል -ኢመደአ
Feb 8, 2026 18
አዲስ አበባ፣ የካቲት 1 /2018 (ኢዜአ) ፦የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) በስድስት ወራት ከተሞከሩ 27 ሺህ 773 የሳይበር ጥቃቶች 99 ነጥብ 03 በመቶ የሚሆነውን ማክሸፍ ተችሏል አለ። ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሂዷል። የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተቀያየሩ የመጡትን የሳይበር ጥቃት ባህሪያት ግምት ውስጥ በማስገባት የመከላከል አቅማችን እየዘመነ ይገኛል ብለዋል፡፡ የሳይበር ደህንነት ሥጋቶችን ቀድሞ ለመለየትና ምላሽ ለመስጠት የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶችን ለማበልጸግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራተጂ መሠረት የሚሆኑ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው የመንግሥት ተቋማትን ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ አሠራራቸውን ዲጂታላይዝ የሚያደርጉ የቴክኖሎጂዎችን እንዲታጠቁ መደረጉን ገልጸዋል። ለአብነትም ገቢዎች ሚኒስቴር የኢ-ኢንቮይስ፣ አዲስ አበባ ገቢዎች የሰውነት ላይ ካሜራ፣ እንዲሁም ፌደራል ፖሊስ የተቀናጀ የሰው ሀብትና የሰነድ አስተዳደር ሲስተሞችን በማልማት አገልግሎታቸውን እንዲያዘምኑ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የሚሰነዘሩ የሳይበር ጥቃቶችን ለማክሸፍ እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ በስድስት ወራት ከተሰነዘሩ 27 ሺህ 773 የሳይበር ጥቃቶች ውስጥ 99 ነጥብ 03 በመቶ የሚሆነውን ማለትም 27 ሺህ 505ቱን ማክሸፍ መቻሉን ገልጸዋል። የዲጂታል ፎረንሲክ ምርመራን በተመለከተ አስተዳደሩ ከቀረቡለት 253 የምርመራ ጥያቄዎች ውስጥ ለ245ቱ ምላሽ መሰጠቱን የኢመደአ መረጃ አመልክቷል፡፡ የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች ፦ https://linktr.ee/ENADigital
በክልሉ የፋይናንስ ስርአቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል እየተሰራ ነው
Feb 8, 2026 36
ከሚሴ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):- በአማራ ክልል የፋይናንስ ስርአቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠንና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በከሚሴ ከተማ እያካሄደ ነው። የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን እንደገለፁት፣ የክልሉን ገቢና ወጭ በማጣጣም ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው።   ለዚህም የፋይናንስ አጠቃቀምን ዲጂታላይዝ በማድረግ በሀብት አጠቃቀምና በሌሎችም አበረታች ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል። በተለይም በመንግስት ግዥ፣ በውስጥ ኦዲት፣ በወጪ አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጡ ግልጸኝነት ያለው አሰራርን በመዘርጋት ለክልሉ ዘላቂ ልማት እንዲውል አግዟል ብለዋል። በክልሉ የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ ለውጡ የፋይናንስ ተቋማትን ማዘመኑ ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደር ልማት ላይ እንዲውል አስችሏል ብለዋል።   በዚህም በዞኑ የተለያዩ የበጀት ምንጮችን በአግባቡ በመጠቀም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል። የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሀብት፣ ንብረትና ግዥ አሰራሩን ማሻሻል ተችሏል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሰላማዊት ነጋ ናቸው። ገንዘብ በአግባቡ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የተጠናከረ ቁጥጥር እየተደረገ ነውም ብለዋል። የሰሜን ጎጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ አቶ በላይነህ ወንድም አፈራሁ በበኩላቸው፣ የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ መቻሉ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስችሏል ብለዋል።   ከዚህ በተጨማሪም ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ለህብረተሰቡ ተአማኒነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚካሄደው መድረክ ላይም የክልሉና የዞን አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊና ግልጽ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እያገዘ ነው
Feb 6, 2026 88
አጋሮ፤ ጥር 29/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊና ግልጽ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እያገዘ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር) ገለጹ። የአጋሮ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬ በይፋ ስራ ጀምሯል። በማስጀመሪያ መድረኩ የተገኙት ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር)፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በየአካባቢው ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ግልጽ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እያገዘ ነው ብለዋል። የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ የመልካም አስተዳደር ችግርን ትርጉም ባለው መልኩ መፍታት እያስቻለና በተለይም የህዝቡን እንግልት ለመቀነስና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ እንደሚጠናከር ገልጸዋል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ በበኩላቸው የክልሉ መንግስት ሕዝቡ ለረጅም ጊዜ ሲያነሳ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ ነው። ከእነዚህ ስራዎች መካከል አንዱ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መሆኑን ጠቅሰው እስካሁንም በሸገር፣ በአዳማ፣ በጅማ፣ በቢሾፍቱ እና በሻሸመኔ ከተሞች መጀመሩን አስታውሰዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀድሞ በተጀመረባቸው ከተሞች አገልግሎቱ የበለጠ እየሰፋ ወደ ክፍለ ከተሞችም እየወረደ መሆኑን ገልጸዋል። በአጋሮ ከተማ አስተዳደር የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ዘመናዊ እና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እድል ይፈጥራል ብለዋል። የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ስራ መጀመር በከተማ አስተዳደሩ ሲነሳ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የሚያግዝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአጋሮ ከተማ ከንቲባ ነዚፍ መሀመድ አሚን ናቸው። የአንድ ማዕከል አገልግሎቱን ወደ ስራ ለማስገባት ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ስፖርት
ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ትኩረት ተሰጥቷል-ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
Feb 8, 2026 47
አዳማ፤ የካቲት 1/2018 (ኢዜአ)፦ስፖርትን ለስነ ምግባር ግንበታና ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ያለውን እቅም ለማሳካት ትኩረት መሰጠቱን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለፁ። ሀገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች ስፖርት ስልጠና ምዘና ውድድር "የተተኪ ስፖርተኞች ልማት፤ ለስፖርታችን እድገት" በሚል መሪ ሐሳብ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ዛሬ ተጀምሯል።   የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በወቅቱ ስፖርትን ለስነ ምግባር ግንባታና ተተኪዎችን ለማፍራት ያለውን አቅም ለማሳካት ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ስፖርትን ለሀገር ገፅታ ግንባታና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ሚናን ለማጉላት እንዲቻል በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራትም የምልመላና ስልጠና ስርዓት ከመዘርጋት ጎን ለጎን ለስፖርት መሰረተ ልማት ተደራሽነት ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።   ባለፉት ስምንት ዓመታት 17 ሺህ 636 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በሀገሪቷ ተገንብተው ለታዳጊዎች የአካልና የአእምሮ ብቃት ማጎልበቻ አገልግሎት እንዲውሉ መደረጉን ገልጸዋል። ዛሬ በአዳማ የተጀመረው ውድድርም ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።   የኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ ሮዛ ቢያ እንደተናገሩት፥ ክልሉ ለስፖርት ልማት ዘርፍ ትኩረት በመስጠት ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው። የስፖርት ልማትን ለማሳካት የክልሉ ከተሞችና ወረዳዎች የስፖርት ማዘወተሪያዎችን ከኮሪደር ልማት ጋር በማቆራኘት እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ዛሬም በ15 የስፖርት አይነቶች ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡ ከ3ሺህ በላይ ታዳጊዎች በውድድር እየተሳተፉ ይገኛሉ ብለዋል።   የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው ከተማዋን ለነዋሪው ምቹ ለማድረግ የስፖርትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች እየተገነቡ ይገኛሉ ብለዋል። ታዳጊዎች በአእምሮና በአካል ብቁ እንዲሆኑ የመዝናኛና ስፖርት ስፍራዎች በከተማዋ በስፋት እየተገነቡ መሆኑን አስረድተዋል። የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች ፦ https://linktr.ee/ENADigital
ፒኤስጂ እና ማርሴይ ዛሬ የሚያደርጉት የደርቢ ጨዋታ ይጠበቃል
Feb 8, 2026 65
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):- በፈረንሳይ ሊግ አንድ 21ኛ ሳምንት ፒኤስጂ ከማርሴይ ይጫወታሉ። ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ከ45 በፓርክ ደ ፕሪንስ ስታዲየም ይካሄዳል። ፒኤስጂ በ48 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ማርሴይ በ39 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የፓሪሱ ክለብ ፒኤስጂ በሊጉ 20 ጨዋታዎችን አድርጎ 15ቱን ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ ሶስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በ20 ጨዋታዎች 43 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 16 ጎሎችን አስተናግዷል። ተጋጣሚው ማርሴይ በበኩሉ በውድድር ዓመቱ ካከናወናቸው 20 ጨዋታዎች መካከል በ12ቱ ድል ሲቀናው አምስት ጊዜ ተሸንፏል። በቀስታ ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 46 ግቦችን ሲያስቆጥር 22 ተቆጥረውበታል። ማርሴይ በሊጉ ከፍተኛ የግብ መጠን ያስቆጠረ ቡድን ነው። ሁለቱ ክለቦች በፈረንሳይ ሊግ 1 ሲገናኙ የዛሬው ለ45ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 44 ጨዋታዎች ፒኤስጂ 26 ጊዜ ሲያሸንፍ ማርሴይ በ10ሩ ድል ቀንቶታል። ስምንት ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። ባለፉት አምስት የሊግ የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ፒኤስጂ አራትት ጊዜ ሲያሸንፍ ማርሴይ አንድ ጊዜ ድል ቀንቶታል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ "Le Classique" የሚል ስያሜ አለው።   የሁለቱ ቡድኖች ከእ.አ.አ 1970ዎቹ መጀመሪያ አንስቶ ታሪካዊ ተቀናቃኝነት አላቸው። ፒኤስጂ በፈረንሳይ መዲና ፓሪስ የሚገኝ እና የሀብታሞች ከተማ እየተባለ ይጠራል። የወደብ ከተማ የሆነችው ማርሴይ የሰራተኛ ማህረሰብ የሚኖርባት እና በከተማቸው ጉዳይ ወግ አጥባቂ የሚባሉ ዜጎች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ይህ ከእግር ኳሱ ባለፈ የፖለቲካና የኢኮኖሚው ጉዳይ ተቀናቃኝነቱን የበለጠ አጋግሎታል። ፒኤስጂ የፈረንሳይ ሊግ አንድ 13 ጊዜ አሸንፏል። ባለፉት ዓመታት በሊጉ የበላይነቱን ይዟል። ክለቡ የወቅቱ የሊጉ የዋንጫ ባለቤት ነው። ተቀናቃኙ ማርሴይ ዘጠኝ ጊዜ ሊጉን ማሸነፍ ችሏል። የሊግ ውድድሩን ለመጨረሻ ጊዜ ያሸነፈው እ.አ.አ 1988/89 የውድድር ዓመት ነው። ሁለቱ ክለቦች የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግን ያነሱ የፈረንሳይ ክለቦች ናቸው። ፒኤስጂ የወቅቱ የውድድሩ የዋንጫ ባለቤት ነው። የዛሬው ጨዋታ ፒኤስጂ መሪነቱን ከሌንስ ለመረከብ፣ ማርሴይ በአውሮፓ መድረክ የመሳተፍ ህልሙን ለማስቀጠል የሚያደርጉት ነው። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት የሊግ ጨዋታ ማርሴይ በናይፍ አገርድ ግብ 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የ33 ዓመቱ ዊሊ ዴላጆድ ተጠባቂውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የዘንድሮው የፈረንሳይ ሊግ 1 ክስተት የሆነው ሌንስ በ49 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው።
ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የግማሽ ማራቶን የጎዳና ላይ ሩጫ በሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ተካሄደ
Feb 8, 2026 81
ሀዋሳ ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):-ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የግማሽ ማራቶን የጎዳና ላይ ሩጫ በሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ተካሄደ። ከአንኮበር እስከ ሀረር በሚል የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የሩጫ ውድድር በተለያዩ ከተሞች እየተካሄደ ይገኛል። በሀዋሳ ሃይቅ ዳርቻ ዛሬ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር የአዲስ አበባ ፖሊስ አትሌቶቹ ስማቸው ወልዴ ወንዶች እና ቤተልሄም አስማረ በሴቶች አሸናፊ ሆነዋል።   በወንዶች በግል የተወዳደሩት አትሌት ጌታቸው ኪዳኔ እና ሱልጣን አብደላ በቅደም ተከተል 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል። በሴቶች ትነበብ ነጋ ከአዲስአበባ ፖሊስ፤ ያተኔ ኮሞሼ ከኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘው ውድድሩን አጠናቀዋል። በግማሽ ማራቶን ከተደረገው የሁለቱም ጾታ አትሌቶች ውድድር በተጨማሪ በአንጋፋ አትሌቶች፣ እንዲሁም በታዳጊዎችና በህጻናት የአራት ኪሎሜትርና የአዋቂዎች የ8 ኪሎሜትር ውድድር ተከሂዷል።   ከአትሌቶች አንደኛ ለወጡት የ100 ሺህ ብር፤ ለሁለተኛ 50ሺህ ብር፤ ሶስተኛ ለወጡት የ15 ሺህ ብር ሽልማት ተሰጥቷቸዋል። ከአንኮበር እስከ ሀረር በሚል እየተካሄደ ያለው የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የሩጫ ውድድር በቀጣይ በጅማ፣ አርባምንጭ፣ በቆጂና ሀረር ከተሞች እንደሚካሄድ ተጠቁሟል። በኢትዮ ቴሌኮም ስያሜ የተካሄደው የሀዋሳ ሀይቅ ግማሽ ማራቶን ውድድር ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት መሆኑ ተገልጿል።
ሊቨርፑል እና ማንችስተር ሲቲ የሚያደርጉት የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ 
Feb 8, 2026 82
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2018(ኢዜአ):- በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሊቨርፑል እና ማንችስተር ሲቲ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ጨዋታው ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም ይካሄዳል። ሊቨርፑል በውድድር ዓመቱ ባደረጋቸው 24 ጨዋታዎች 11 ጊዜ ድል ሲቀናው ሰባት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ ስድስት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 39 ግቦችን በጨዋታዎቹ ላይ ሲያስቆጥር 33 ጎሎችን አስተናግዷል። በ47 ዓመቱ ኔዘርላንዳዊ አርን ስሎት የሚመራው ሊቨርፑል በ39 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ማንችስተር ሲቲ በሊጉ እስከ አሁን ባካሄዳቸው 24 ጨዋታዎች 14 አሸንፎ በአምስቱ ተሸንፎ በተመሳሳይ አመስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 49 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 23 ግሎች ተቆጥረውበታል። በ55 ዓመቱ ስፔናዊ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንችስተር ሲቲ በ47 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።   ሁለቱ ክለቦች በሁሉም ውድድሮች እስከ አሁን 199 ጊዜ የተገናኙ ሲሆን ሊቨርፑል 95 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ማንችስተር ሲቲ 51 ጊዜ ሲያሸንፍ 53 ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። በፕሪሚየር ሊጉ 57 ጊዜ ተገናኝተው ሊቨርፑል 23 ጊዜ ሲያሸንፍ ማንችስተር ሲቲ 13 ጊዜ ድል ቀንቶታል። 21 ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥተዋል። በ24ኛ ሳምንት ኒውካስትል ዩናይትድን 4 ለ 1 በማሸነፍ ከአምስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል የተመለሰው ሊቨርፑል የዛሬው ጨዋታ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለመሳተፍ ለሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ነው። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል በዘንድሮው የውድድር ዓመት ወጥነት የሌለው ብቃት እያሳየ ይገኛል። በሊጉ የ24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከቶተንሃም ሆትስፐርስ ጋር ሁለት አቻ የወጣው ማንችስተር ሲቲ በዋንጫ ፉክክሩ ለመቆየት የዛሬው ድል ያስፈልገዋል። ማንችስተር ሲቲ ካሸነፈ የሊጉ መሪ አርሰናል ጋር የሚኖረው የግብ ልዩነት ወደ ስድስት ዝቅ ይላል። የ46 ዓመቱ ክሬግ ፖውሰን ተጠባቂውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ብራይተን ከክሪስታል ፓላስ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ በአሜክስ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በጋምቤላ ክልል የሙቀቱ መጠን እየጨመረ በመምጣቱ በመንግስት የስራ ስዓት ላይ ለውጥ ተደረገ
Feb 7, 2026 86
ጋምቤላ፤ ጥር 30 /2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የሙቀቱ መጠን እየጨመረ በመምጣቱ የመንግስት የስራ ስዓት ላይ ለውጥ መደረጉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና ካቢኔ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ኡቶው ኡኮት፤ የሙቀቱ መጠን እየጨመረ በመምጣቱና ለስራ አስቸጋሪ በመሆኑ ከፊታችን ሰኞ የካቲት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የስራ ሰዓት ለውጥ መደረጉን ገልጸዋል። የተደረገው የሰዓት ለውጥ ለቀጣዮቹ ሶስት ወራት የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመው በዚሁ መሰረት ሁሉም የመንግስት ተቋማት ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። በለውጡ መሰረትም ቀደም ሲል ከጧቱ 1:00 እስከ 6: 30 የነበረው ከ1:00 አስከ 5:30 እንዲሆን እንዲሁም ከስዓት በኋላ ከ9:00 እስከ 11:30 የነበረው 10:00 እስከ 12:30 ይሆናል ብለዋል። የስራ ስዓት ለውጡ ወይና ደጋ የአየር ንብር ያላቸውን የመንጌሽና የጎደሬ ወረዳዎችን እንደማይጨምር የገለጹት ኃላፊው የክልሉ የመንግስት ሰራተኛች በተጠቀሰው ጊዜ ወደ ቢሮ በመግባት ስራቸውን በትጋት እንዲያከናውኑ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ሜትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋምቤላ ክልል የሜትሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል ተወካይ ነብዩ ፈረደ፤ በአሁኑ ወቅት የክልሉ አማካይ የቀኑ ከፍተኛ የሙቀት መጠን 41.4 ድግሪ ሴልሸስ መሆኑን ጠቁመዋል። የሌሊቱ ዝቅተኛው የሙቀት መጠን ደግሞ 25 ነጥብ 6 ድግሪ ሴልሸስ መሆኑን ጠቁመው ባለፉት ወራት የቀኑ ከፍተኛ የሙቀት መጠን በአማካኝ ከ35 ድግሪ ሴልሸስ የለሊቱ ደግሞ 22 ዲግሪ ሸልሰስ በታች እንደነበር አስታውሰዋል። በክልሉ የሞቃታማ ወራት የሚባሉት የካቲት፣ መጋቢትና ሚያዚያ ወራት ሲሆኑ በእነዚህ ወራት ውስጥ የቀኑ ከፍተኛ የሙቀት መጠን እስከ 45 ድግሪ ሴልሸስ የሚደርስበት ጊዜ እንዳለ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በምዕራብ ሐረርጌ ዞን አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የበጋ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው
Feb 7, 2026 84
ጭሮ፤ ጥር 30/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ከ700 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የበጋ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። በዞኑ እየተከናወነ ያለውን የበጋ የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተመለከተ ኢዜአ የሚመለከታቸውን የስራ ሃላፊዎችና የልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮችን አነጋግሯል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ ዞን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ሃላፊ ሸረፍ አብደላ፤ በዞኑ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በተለይም ተራቁተው የቆዩ ተራራማ አካባቢዎች እንዲያገግሙ ማድረጉን ገልጸዋል።   በልማቱ የተገኘውን ውጤት ተከትሎ በበጋና ክረምት ጭምር የልማት ስራው ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም መሰረት በዘንድሮው የበጋ ወራት ከ700 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በ455 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በልማቱ እስካሁን ከ109 ሺህ 700 ኪሎ ሜትር በላይ የአፈርና የድንጋይ እርከን ስራ በማከናወን የእቅዱን 95 በመቶ ማሳካት የተቻለ መሆኑን ተናግረዋል።   ከልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር ጀማል አብዶ፣ ወይዘሮ ነስራ አብዱሬ እና አብነት ጉልላት፤ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራው አካባቢን ከመጠበቅም ባለፈ ለምርታማነት መጨመር ትርጉም ያለው በመሆኑ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።   የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነትን ከማሳደግም ባለፈ የጎርፍ አደጋን ለመከላከል ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ተናግረው አጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል።
የተፋሰስ ልማት ስራ የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርትና ምርታማነታችንን አሳድጎልናል- አርሶ አደሮች
Feb 6, 2026 88
ወላይታ ሶዶ ፤ ጥር 29/2018 (ኢዜአ)፡- የተፋሰስ ልማት ስራው የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርትና ምርታማነታቸውን ማሳደጉን በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ አርሶ አደሮች ተናገሩ። በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ነዋሪ የሆኑ አርሶ አደሮች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ እየተካሔደ ያለው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ የመሬት ለምነትን በመመለስ ምርታማነት ለማሳደግ እያስቻለ ነው።   በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ኦፋ ወረዳ ነዋሪ አቶ ተስፋዬ ሜጊሶ እና ማርታ አዋሾ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ መጀመሩ በጎርፍ እየተጠረገ ይወሰድ የነበረውን ለም አፈር ጥቅም ለይ ለማዋል አስችሎናል ይላሉ።   በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው ሳቢያ የደረቁ ምንጮች ዳግም እንዲፈልቁ በማድረጉ የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲለሙ ማድረጉን አመልክተዋል።   በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ምስራቅ ባድዋቾ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አበራሽ አቡቶ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሰራው የተራቆጡ አካባቢዎች ዳግም እንዲለሙ ማድረጉን ተናግረዋል ። በዚህም የተለያዩ የጓሮ አትክልት በማምረት ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ጠቅሰው የተፋሰስ ልማት ስራን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው ያመለከቱት ።   በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ፋኖሴ መኮንን በበኩላቸው፤ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራው ምርታማነት በማሻሻል ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ነው። ባለፉት ዓመታት በተሰራው ስራ እንደ ሀገር አደጋ ላይ ከነበሩ 54 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ውስጥ 33 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው ዳግም እንዲያገግም ለማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።። በተለይም የአፈር ለምነትን በመጨመር፣ የደረቁ ምንጮች ዳግም እንዲፈልቁ በማድረግ እና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ጉልህ ሚና መጫወቱንም ነው ያነሱት።   የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራው እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማሳካት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዘንድሮው ዓመትም 25 ሚሊዮን የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በ23 ሺህ ተፋሰሶች ላይ 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው የተፋሰስ ልማት ስራ ላይ እየታየ ያለው የህብረተሰብ የተሳትፎ ባህል መጠናከር እንደሚገባውም አሳስበዋል።
የሐረማያ ሐይቅ የቱሪስት መዳረሻነት የማበልጸግ ስራ በተቀናጀ መንገድ በመከናወን ላይ ይገኛል
Feb 2, 2026 171
ሐረማያ ፤ጥር 25/2018 (ኢዜአ) ፡-የሐረማያ ሐይቅን የቱሪስት መዳረሻነቱን የማበልጸግ ስራ በተቀናጀ መልኩ እየተካሔደ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ። በማያ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙት የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል የሐረማያ ሃይቅ እንዱ ነው። ለበርካታ ዓመታት ደርቆ የነበረው ሐይቁ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች ትኩረት ተደርጎ በመከናወናቸው ወደ ቀድሞው ይዞታው መመለስ ችሏል። የከተማ አስተዳደሩ እና የአካባቢው ማህበረሰብ ሃይቁን እያለማውና እየተንከባከበው በመሆኑም የጎብኚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ጀሚላ ሲምቢሩ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ሐይቁ ከመዝናኛነቱ ባለፈ ለወጣቶች የስራ እድል እየፈጠረ የሚገኝ ሲሆን በዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የማጎልበት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። አካባቢው ትልልቅ እሴቶችና ጸጋዎች የሚገኙበትና በኪነ ጥበቡም ዘርፍ ስመ-ጥር አርቲስቶች የፈለቁበት መሆኑንም ይገልፃሉ። የአካባቢውን ባህል፣ ኪነ ጥበቡብና ቱሪዝሙ ዘርፉን እንደ አንድ ጸጋ በመጠቀምና ከቱሪዝም ጋር በማሰናሰል የዘርፉን ኢኮኖሚ ማሳደግና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።   የማያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢፍራህ ወዚር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በአፈርና ውሃ ጥበቃ እና በአረጓዴ አሻራ ስራ የተመለሰውን የሐረማያ ሃይቅ አጠቃቀምን የማስተካከል፣ የመጠበቅና የመንከባከብ ስራ እየተከናወነ ይገኛል። ሐይቁ ወደ ቀድሞ ቦታው መመለሱ ለጎብኚዎች እርካታን ከማጎናጸፉ ባለፈ ለአካባቢው ነዋሪዎችና ለወጣቶች የገቢ ምንጭ እየሆነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የሐረማያ ሐይቅ በተደረገለት እንክብካቤ ውብና ማራኪ የቱሪስት ቀልብ የሚስብ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፤ ለወጣቶችም የገቢ ምንጭ ማግኛ ሆኗል ያለው ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የቱሪዝም ባለሙያ ኦሊያድ በሪሶ ናቸው።   በአካባቢው ባለሀብቶችን በመጋበዝ ሎጆችና ሪዞርቶች በማስፋፋት የተሻሉ ስራዎችን መስራት እንደሚቻልም ነው አቶ ኦሊያድ አስተያየታቸውን የሰጡት።   በሐረማያ ሐይቅ ላይ የጀልባ አገልግሎት የሚሰጠው ወጣት ሙርቲ አህመድ፤ጎብኚዎችን በጀልባ ከማስጎብኘት ስራ በተጨማሪ በአሳ ልማት ስራም መሰማራቱን ይገልፃል።    
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ የምታስተናግዳቸው አህጉራዊ ሁነቶች
Feb 4, 2026 278
በሙሴ መለሰ የዓለም ስርዓት በፍጥነት እየተቀያየረ ይገኛል። አፍሪካ በዚህ ተለዋዋጭ ስርዓት ውስጥ የሚገባትን ቦታ የመያዝ ጉዳይ የመነጋገሪያ አጀንዳ ከሆነ ሰነባብቷል። አፍሪካ በርካታ ወጣት የያዘች እና ብዝሃ የተፈጥሮ ፀጋዎች ያሏት አህጉር ናት። በአፍሪካ ተግባራዊ የተደረገው አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በቀጣናው የንግድ ትስስርን በማሳለጥ እድገትን የማፋጠን ተስፋ ተጥሎበታል። አፍሪካ እድሎቿን በሚገባ ለመጠቀምና የሚስተዋሉ ፈተናዎቿን ለመሻገር ምላሽ የምትሰጥበት የልማት እና እድገት ጉዞዋን ከመበየን ባለፈ በዓለም መድረክ የሚኖራትን ሚናም ይወስናል። በአህጉር ደረጃ የተቀመጡ እንደ አጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ያሉ አህጉራዊ ማዕቀፎች እንዲሳኩ ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። መንግስታት፣ የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮች ትብብራቸው ማጠናከር ይኖርባቸዋል።   የተገቡ ቃልኪዳኖችን ወደ ሚለካ ውጤት ለመቀየር ዘላቂነት ያለው አመራር ሰጪነት፣ ኢንቨስትመንትን ማጠናከር እና ተከታታይነት ያለው ውይይቶችን ማድረግ ይገባል። ውሳኔ ሰጪዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኙ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ መድረኮች በአጀንዳዎች ላይ የተቀናጀ የተግበባር ምላሽ ለመስጠት ቁልፍ ሚና አላቸው። አፍሪካ እድሎቿን በመጠቀም እና ፈተናዎቿን በማለፍ መንገድ ላይ በሆነችበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ ሁለት ወሳኝ አህጉራዊ ሁነቶችን ታስተናግዳለች። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የመሪዎች ጉባኤ መሪ ሀሳብ ነው።   ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። የመሪዎች ጉባኤው በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ያስተላልፋል ተብሎም ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ኮሚቴ ተወካዮች (PRC) ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ መክሯል።   ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን አቅርቧል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። ከአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ማግስት ሌላኛው በኢትዮጵያ የሚካሄደው ዘጠነኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ነው። የቢዝነስ ፎረሙ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(ኢሴኤ) ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሁነቱን አዘጋጅተውታል። “የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ በፋይናንስ መደገፍ፤ ስራ እና ኢኖቬሽን ለዘላቂ ትራንስፎርሜሽን” የፎረሙ መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም በአፍሪካ የልማት እና የኢኮኖሚ እድገት ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን በማድረግ በየዓመቱ የሚካሄድ ከፍተኛ አህጉራዊ የምክክር መድረክ መሆኑን የኢሲኤ መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ አጋርነትና የኢንቨስትመንት መጠንን ማሳደግ በተለይም የመንግስት እና የግል የተቀናጀ የፋይናንስ አቅርቦትን ጨምሮ የተለያዩ የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይወያያል። የወጣቶችን የኢኖቬሽን ስራ ከፋይናንስ አቅርቦት ጋር የሚያስተሳስር የአፍሪካ የወጣቶች አይበገሬነትና ትራንስፎርሜሽን ማዕቀፍ ይፋ ይሆናል። በኢሲኤ የበለጸገውና የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ ቃል ኪዳኖችን ትግበራ የሚከታታልና የሚቆጣጠር ስርዓትም በፎረሙ ይፋ ሆኖ ወደ ትግበራ ይገባል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው ሁነት ላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የምክክር መድረኮችና የባለሙያዎች ውይይቶች ይደረጋሉ።   አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጣራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ አውደ ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። ከአህጉራዊ ሁነቶቹ ባሻገር የባለብዙ ወገን መድረክ የሆነው የአፍሪካ እና ጣልያን ጉባኤ የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ሁነቶቹን ማዘጋጀቷ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ጸንቶ የቆየውን የመሪነት ሚናዋን እንዲሁም የአህጉራዊ ምክክር፣ የባለብዙ ወገን ውይይቶችና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባት ማዕከልነቷንም አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ በኮሪደር ልማት እና በከተማ ማዘመን ስራ በፍጥነት እየተለወጠች ሲሆን የሁነቱ ተሳታፊዎች ከስብሰባው ባለፈ የመዲናዋን አዲስ መልክ የመመልከት እድል ያገኛሉ። የእነዚህ አህጉራዊ ስብሰባዎች ስኬት የሚለካው በአቋም መግለጫ ሳይሆን አጋርነትን በማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና የሚጨበጥ ውጤት በአህጉሪቱ በማስመዝገብ ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ የምታዘጋጃቸው አህጉራዊ ሁነቶች አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጣራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ አውደ ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። ከአህጉራዊ ሁነቶቹ ባሻገር የባለብዙ ወገን መድረክ የሆነው የአፍሪካ እና ጣልያን ጉባኤ የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ሁነቶቹን ማዘጋጀቷ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ጸንቶ የቆየውን የመሪነት ሚናዋን እንዲሁም የአህጉራዊ ምክክር፣ የባለብዙ ወገን ውይይቶችና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባት ማዕከልነቷንም አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ በኮሪደር ልማት እና በከተማ ማዘመን ስራ በፍጥነት እየተለወጠች ሲሆን የሁነቱ ተሳታፊዎች ከስብሰባው ባለፈ የመዲናዋን አዲስ መልክ የመመልከት እድል ያገኛሉ። የእነዚህ አህጉራዊ ስብሰባዎች ስኬት የሚለካው በአቋም መግለጫ ሳይሆን አጋርነትን በማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና የሚጨበጥ ውጤት በአህጉሪቱ በማስመዝገብ ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ የምታዘጋጃቸው አህጉራዊ ሁነቶች አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች።
በኒጀር በደረሰ ጥቃት መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው የአስካይ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ተጠግነው በቅርቡ አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ
Feb 3, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦ በኒጀር ዋና ከተማ በደረሰ ጥቃት መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት የአስካይ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ተጠግነው በቅርቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ ፡፡ አየር መንገዱ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው ማብራሪያ ባለፈው ሐሙስ ጥር 21/ 2018 ዓ.ም ሌሊት በኒጀር ዋና ከተማ ኒያሚ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰው ጥቃት ሁለት የአስካይ አየር መንገድ ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ፡፡ አውሮፕላኖቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አጋር የሆነው የአስካይ አየር መንገድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት ከአውሮፕላን አከራዮች የተከራያቸው እና በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የተመዘገቡ መሆናቸውን አስረድቷል፡፡ በአውሮፕላኖቹ ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመገምገም የተላከው የቴክኒክ ቡድን ጉዳቱ መጠነኛ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን አውሮፕላኖቹ ተጠግነው በቅርቡ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡም ተገልጿል ::
የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም አጋርነታቸውን ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Feb 2, 2026 151
አዲስ አበባ፤ጥር 25/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም ሰላምና ልማትን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች አጋርነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር ጋር በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተወያይተዋል። ውይይቱ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ በቆየው የአፍሪካ እና ዩናይትድ ኪንግደም አጋርነት ያተኮረ ነው። ሁለቱ ወገኖች የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እና ህግን መሰረት ያደረገ ዓለም አቀፍ ስርዓት ለመጠበቅ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።   የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ዩናይትድ ኪንግደም ከአፍሪካ ጋር ያላትን የረጅም ጊዜ ትስስር ያደነቁ ሲሆን በዓለም ላይ ያላትን ገንቢ ሚና እና ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ጋር በጤና፣ ትምህርት፣ የአየር ንብረት ምላሽ እና ንግድ ያላትን ትብብር አንስተዋል። ሀገሪቷ ለአፍሪካ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) በአደጋ ጊዜ ዝግጁነት እና ምላሽ እንዲሁም በሶማሊያ ለአፍሪካ ህብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) ድጋፍ እያደረገች እንደምትገኝም አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር የአፍሪካ ህብረት በዓለም ዲፕሎማሲ፣ ቀጣናዊ ሰላም እና ልማት ያለውን ሚና አድንቀዋል። ሁለቱ ወገኖች የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም በሱዳን፣ በሳሄል ቀጣና እና በሶማሊያ ያለውን የአፍሪካ ህብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሀገራት ለውኃ አቅርቦት፣ ጥራት እና ለንጽህና መሰረተ ልማቶች ቅድሚያ መስጠት ይጠበቅባቸዋል
Feb 1, 2026 270
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ሁሉም ሀገራት ለውኃ አቅርቦት፣ ለጥራት እና ለንጽህና መሰረተ ልማቶች ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው የአፍሪካ ሕብረት አስገነዘበ። በሕብረቱ የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ጥበቃ ኮሚሽነር ሙሴ ቪላካቲ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አህጉራዊው የግብርና ልማት ፕሮግራም ባለፉት 20 ዓመታት በአባል ሀገራት ዘንድ ጉልህ ለውጦች ማምጣቱን ገልጸዋል።   ይህም አባል ሀገራት ጠንካራ የግብርና ዕቅድ ሥርዓት እንዲዘረጉ፣ ውጤታማ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም ቀረፃ እንዲኖራቸው እና በምርትና ምርታማነት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማገዙን አንስተዋል። ፕሮግራሙ ትኩረት የሚያደርገው በተለይም በምርት መጠንና በምርታማነት ዕድገት ላይ በመሆኑ፤ በአሁኑ ወቅት በበርካታ ሀገራት ውስጥ የሚታየው የምርት መጠን መጨመር የዚሁ ጥረት ውጤት ነው ብለዋል። ማንኛውም የልማት እንቅስቃሴ ከውኃ ጋር የተቆራኘ መሆኑን አስገንዝበው፤ ግብርናን፣ ኢነርጂን ወይም ጤናን ስናስብ ሁሉም ነገር ከውኃ ጋር የተያያዘ ነው፤ ስለዚህ ውኃ ለዘላቂ ልማት እጅግ ወሳኝ ነው ብለዋል።   ለዚህም ነው “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የሚለው መሪ ሐሳብ ለ39ኛው የሕብረቱ መሪዎች ጉባዔ የተመረጠው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ጉዳዩ በሕብረቱ አጀንዳነት የተያዘው በአህጉሪቱ ያለውን የውኃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል። በአህጉሪቱ ወደ 400 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች መሰረታዊ የውኃ አገልግሎት እንደማያገኙ ጠቁመው፤ ከ700 ሚሊየን የሚልቁትም ደኅንነቱ የተጠበቀ የጽዳት አገልግሎት የላቸውም ብለዋል። ይህ የአገልግሎት እጥረት በሰዎች የዕድገትና የአህጉሪቱ የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ትልቅ እንቅፋት መሆኑንም አመላክተዋል። ውኃን እንደ ትምህርት፣ ጤና እና ግብርና ትልቅ ትኩረት ሰጥተን ብንሠራበት ኖሮ ይህንን ችግር በቀላሉ መፍታት እንችል ነበር ያሉት ኮሚሽነሩ፤ አሁን ላይ ጉዳዩ ትኩረት በማግኘቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።   በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ዋነኛ ግብ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መሆኑን ተናግረው፤ የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮግራም 45 በመቶ የሚሆነውን የግብርና ምርት በአፍሪካ ለማምረት ግብ ይዞ እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። በተጨማሪ የአፍሪካን የውኃ አካላት ሀብት ወይም ብሉ ኢኮኖሚን ሙሉ በሙሉ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሆነ አንስተው፤ ይህ ዘርፍ ለአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራና ለኢኮኖሚ መነቃቃት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል ነው ያሉት። የአፍሪካን የሰብል ዝርያዎች መጠበቅ መቻል የአህጉሪቱ ኅልውና ጉዳይ መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸው፤ ለዚህም ጠንካራ የዘር ባንኮች ሊኖሩን ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
ሐተታዎች
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 446
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ።   በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 783
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 735
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 956
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 798
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 773
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1363
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3667
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3329
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2173
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7978
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6466
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60099
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54081
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34688
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32250
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27527
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26489
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26022
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25817
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60099
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54081
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34688
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32250
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!!
Feb 6, 2026 111
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በያንተስራ ወጋየሁ -ዲላ ቀን ቀንን እየወለደ ጊዜ ሳያቋርጥ እንደ ዥረት መፍሰሱን አያቆምም። ትናንት አዲስ የነበረው አሮጌው የሚባልበት፣ ዛሬ አዲስ ሆኖ ነገ አሮጌ ለመባል ይሮጣል። ወቅቶች ይፈራረቃሉ፣ ይመሻል፣ ይነጋል፣ ትናንት ለዛሬ፣ ዛሬ ለነገ እንዲህ እንዲህ እየተቀባበሉ ዘመን ዘመንን እየተካ ዛሬ ላይ ተደርሷል።   በጥምር ግብርናውና በቡናው የሚታወቀው ጌዴኦ ትናንትን ሸኝቶ ዛሬን እንደ አዲስ ለመቀበል ሽር ጉድ እያለ ነው። በክረምቱ የተዘራው ሰብል ተሰብስቦ ወደ ጎተራ እንዳስገባ ጌዴኦ አዲስ ዓመቱን ‹‹ዳራሮ››ን ይቀበላል። ዳራሮ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ቂም የያዘ ቂምና ቁርሾውን የሚተውበት፣ ወጣቶች የሚተጫጩበት፣ አዛውንቶች ወደ ሽምግልና የሚሸጋገሩበት እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው።   "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው የጌዴኦ አርሶ አደር ካመረተው ምርት ለመሪው፣ ልጆች ለወላጆችና ለአሳዳጊዎቻቸው፣ አዲስ ተጋቢዎች ለአማቾቻቸው፣ ቂም የያዘ ሰው እንዲሁ የተቀየመውን ሰው ይቅርታ ለመጠየቅ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። "ጉማታ" በጌዴኦ ዘመን መለወጫ ወቅት የሚፈጸም ስጦታ ነው። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማኅበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ነው። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። በዳራሮ በዓል አከባበር ውስጥ "ጉማታ" እጅግ አስፈላጊና ትልቅ ትርጉም ያለው ባህላዊ የክብር ስጦታ የመስጠት ሥርዓት ነው። "ጉማታ" ማለት በቀጥታ ትርጉሙ "ስጦታ" ማለት ቢሆንም፣ በጌዴኦ ባህል ግን ከስጦታ በላይ ነው። ምስጋናን፣ ፍቅርን፣ አክብሮትንና በረከትን የመጋራት መገለጫ ነው።   የጌዴአ ባህላዊ የባሌ ስርዓት መሪ ሆነው የሚሰየሙት አባ ገዳ ለህዝብ ከመጸለይ፣ ከማስታረቅና ክፉን በማውገዝ ህዝቡ ተፈጥሮን እንዲንከባከብ ከማስተማር ውጭ አይዘሩም፣ አይነግዱም፣ አልፎም እንሳስትን አያረቡም፡፡ የዳራሮ በዓልን ተከትሎ ህዝቡ የሚያቀርብላቸውን "ጉማታ" በመቀበል ባህላዊ የመሪነት ሚናቸውን በአግባቡ ከመወጣት ውጪ። ኑሮው ከጥምር እርሻ ጋር የተቆራኘው የጌዴኦ ሕዝብ ዘርቶ ካጨደው፣ አርብቶ ካገኘው ከብት፣ አንቦ ከቆረጠው ማር፣ ከሁሉም በአይነት በአይነቱ ሸክፎ ዳራሮ ወደ ሚከበርበት ሶንጎ (አደባባይ) ይተማል። ለጉማታ ከሚቀርቡ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ስጦታዎች አንዱ ማር ነው። ማር በጌዴኦ ዘንድ የጣፋጭ ዘመንና የጤና ምልክት ተደርጎ ይወሰዳልና ዋናው ስጦታ ነው። ጌዶኦዎች ቡና፣ ቅቤና ባህላዊ ምግቦች፣ የቁም እንስሳት በግና ስንጋ እንዲሁም ገንዘብ በመያዝ በበዓሉ ውስጥ የጉማታ ስርዓት ሲደርስ ተሽቀዳድመው ለአባ ገዳው በመስጠት ምርቃት ይቀበላሉ።   "ጉማታ" የተቀበለው ሰው የሚመርቀው ምርቃት በሰጪው ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይታመናልና ከስጦታው ይልቅ ምርቃቱ ትልቅ ዋጋ አለው። "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው ጌዴኦ በረከትን ማካፈል ለቀጣዩ ዓመት ተጨማሪ በረከት እንደሚያገኝ ስለሚያውቅ ጉማታ መስጠት የዘመናት ቅርሱ ነው። ጉማታ ከአባ ገዳና ከባህል ሽማግሌዎች ባለፈ አርሶ አደሩ ከማጋኖ (ከፈጣሪ) ያገኘውን በረከት ለሚወዳቸውና ለሚያከብራቸው ሰዎች የሚያቀርብበት መንገድ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገልጸዋል።   ልጆች ለወላጆቻቸውና ለቤተሰብ አባላት ላሳደጓቸውና ለሰጧቸው ምርቃት ምስጋናቸውን ለመግለጽ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። በቅርቡ ጋብቻ የመሠረቱ ወጣቶች ወደ አማቾቻቸው ቤት ጉማታ ይዞ በመሄድ ዝምድናቸውን ያጠናክራሉ። በዓመቱ ውስጥ ቅሬታ ወይም ቂም ካለ፣ በዳራሮ ወቅት ጉማታ ይዞ በመሄድ ይቅርታ ይጠየቃል። ጉማታ የሰውን ልብ ለማለስለስና አዲስ ዓመትን በሰላም ለመጀመር ያገለግላል ተብሎ ስለሚታመን። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማህበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ስለመሆኑም ነው ዋና አስተዳዳሪው የጠቆሙት። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። ይህም የመደጋገፍ እሴትን ከማጠናከር በተጓዳኝ ህዝቡ የመንግስት ገቢን እንዲሁም በማህበረሰብ ተሳትፎ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆን መሰረት የጣለ ነው ይላሉ።   የዘንድሮው ዳራሮ ከቤት በተለይም ከአባ ገዳው መኖሪያ አንስቶ በሶንጎዎችና በየደረጃው በሚገኙ መዋቅሮች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ጭምር እየተከበረ መሆኑን ያነሱት አስተዳዳሪው ጉማታም ዋናው የበዓሉ እሴት ሆኖ እየተከበረ ነው ብለዋል። ባህልና ማንነትን በማስጠበቅና በማዳበር፣ ባህሉ ወደ ወጣቶች እንዲተላለፍ በማበረታታት እንዲሁም የጌዴኦ ባህልን ለሌሎች ህዝቦች ለማስተዋወቅና የማህበረሰብ አንድነትና ባህላዊ እሴትን ለማጠናከር እያገለገለ ያለው የጌዴኦ ዘመን መለወጫ ዳራሮ ጥር 29 እና 30 በዲላ ከተማ ይከበራል። የዳራሮ በዓል የጌዴኦን ሕዝብ የሥራ ባህል፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ዕውቀትና የሰላም እሴት ለዓለም የሚያሳይ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ይህ በዓል በተለይ የጌዴኦ የባህላዊ መልክዓ ምድር (Cultural Landscape) በዩኔስኮ (UNESCO) በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ተከትሎ፣ አሁን ላይ ከቤትና ከአደባባይ አልፎ ዓለም አቀፋዊ ትኩረት እያገኘ ያለ ታላቅ እሴት ሆኗል። የዓመት ሰው ይበለን!!
ዕድሜ  ያልገደበው የልማት አርበኝነት 
Jan 14, 2026 465
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት ብርቱዎች ነገን በማሰብ ሁሌም ታትረው ይሰራሉ፤ ይደክማሉ፤ ይጥራሉ…ለቀጣዩ ትውልድም ጥሪት በማስቀመጥ አሻራቸውን ያኖራሉ። አገር የምትገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው። “አባት ያበጀው፤ ለልጅ ይበጀው” እንደሚባለው ልጆች ከአባቶቻቸው ያገኙትን ጥሪት በአዲስ እውቀትና አሰራር ለአገር እድገት በሚበጅ መልኩ አጠናክረው መጠቀማቸው አይቀርም። “ዕድሜ ጸጋ ነው” የሚለው አባባል አንዳንዴ በዕድሜ ብንገፋም ጠንክረን ከሰራን ብዙ ነገር እናያለን ከሚለው ጋር የተያያዘ ነው። በሰቆጣ ከተማም እድሜ ሳይገድባቸው በልማት ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ለዚህ ማሳያ ናቸው። የከተማዋ ነዋሪ የ67 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ አወቀ እና የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ዕድሜያቸው ቢገፋም ጠንክሮ ከተሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና ዕድሜ ጸጋ ሆኖ ብዙ ለውጥ ማየት እንደሚቻል ማሳያ ናቸው። ግለሰቦቹ ከዕድሜ ብዛት ጉልበቴ ደከመ፣ አይኔ ፈዘዘ፣ እጄም ተሳሰረ…ሳይሉ ጊዜያቸውን በደን፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ በማሳለፍ ለወጣቶች የልማት አርአያነት ያለው ተግባር እየፈጸሙ ነው። አቶ ብርሃኑ አወቀ በሰቆጣ ከተማ ዳርቻ የሚገኝ አለቱ ያገጠጠና የተራቆተ አካባቢን ከሌላ አካባቢ ለም አፈር በማምጣትና በመደልደል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ደን በማልማት ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ነው።   ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከወጣሁ ጀምሮ ጠንክሬ በመስራት የምለወጥበትን ሥራ ማሰብ ስነበረብኝ፤ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ለዘመናት የቆየን ጭንጫ መሬት ጠርጌና ደልድዬ ማልማት ችያለሁ ይላሉ ወደኋላ መልስ ብለው የተነሱበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ። ግማሽ ሄክታር በማይሞላ መሬት ላይ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ዘይቱና፣ ጌሾ፣ ቡና፣ ማንጎና አቮካዶ አልምተዋል። በተጨማሪም ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና ሽንኩርት በማምረት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ጥሪት አፍርተዋል።   ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ተግቶ መስራት ከተቻለ ሀብት ማፍራትና ህይወትንም መለወጥ እንደሚቻል የገለጹት አቶ ብርሀኑ፣ ወጣቱም ከእሳቸው የሥራ ትጋት በመማር በአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ሊጠቀም ይገባል ሲሉ ይመክራሉ። ሌላው የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ባለፉት 18 ዓመታት በተሰማሩበት የአትክልትና ደን ልማት ሥራ የአካባቢያቸውን ገጽታ ቀይረዋል። የዕድሜ ዘመናቸውን በውትድርናና በመንግስት ሠራተኝነት በማገልገል ሃገራዊ ግዳጃቸውን ሲወጡ ነው የቆዩት።   ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከተገለሉ በኋላም ቤት ውስጥ መቀመጥን አልመረጡት። አካፋና ዶማቸውን ይዘው ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ ጌሾ፣ ዘይቱና እና ማንጎ በማልማት ምርቱን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። በአካባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ለይተን ማልማት ከቻልን ድህነትን ማስወገድ የሚከብድ አይሆንም ያሉት አቶ ታደሰ፣ የተራቆተና በጎርፍ የተጎዳን መሬት በማልማት አካባቢውን ሳቢና ማራኪ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት። ወጣቱም ከእሳቸው አርአያነት ያለው ተግባር በመማር በአካባቢው እጁ ላይ ባለ ሀብት ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ማሳየት እንዳለበት መክረዋል።   የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ እንደገለጹት፤ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 24ሺህ 847 አርሶ አደሮች በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል ዕድሜ ሳይገድባቸው ወደ ልማት የገቡ አረጋዊያን እያከናወኑት ያለው የግብርና ልማት ሥራ ለወጣቱ ትልቅ ትምህርት እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከእነሱ ልምድ በመውሰድ በዞኑ ወጣቶች፣ ሴቶችና አረጋዊያን በጓሮና ባላቸው መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህም በዞኑ የሚስተዋለውን የስርዓተ ምግብ ችግር ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም