አርእስተ ዜና
የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የመደመር ትውልድን ግንባታ እንዲደግፍ ጥሪ ቀረበ
Mar 23, 2023 89
አዲስ አበባ መጋቢት 14/20115 (ኢዜአ)፦ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ባለው ተቋማዊ አቅም የመደመር ትውልድን ግንባታ እንዲደግፍ ጥሪ ቀረበ። አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ መደመር የኢትዮጵያን እምቅ አቅም በማሰባሰብ ሀገርን ወደ ከፍታ ለማሻገር በለውጡ የተወለደ የፖለቲካ ዕይታና ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰዋል።   መደመር ግቡ ያለፉ ጠባሳዎቻችንን ማከም፣ ችግርቻችንን በአገር በቀል እውቀት በጋራ መፍታት ነው ሲሉም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲሱ የመደመር ትውልድ መፅሃፋቸው የመደመር ትውልድ ከትናንት በመማር በጋራ ጥረታቸው ጠንካራዋንና የበለፀገች ኢትዮጵያን መገንባት እንዳለባቸው መክረዋል ብለዋል።   የጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በበኩላቸው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር እሳቤና የመደመር ትውልድ መጻህፍትን ሀገርና ዓለምን ለመጥ ቀም በማሰብ ለንባብ እንዳበቁ ተናግረዋል። መደመር ያለፉ ውስብስብ ሀገራዊ ችገሮችን በጋራ መፍታትን፣ ዓለም ቀፋዊ ትብብር ማጠናከርን የሚያስገነዘብ መሆኑንም ጠቅሰዋል።   ከመጻሕፍቱ ሽያጭ የሚገኘው ገንዘብ ለትውልዱ የሚጠቅሙ ፕሮጀክቶችን በማልማት ላይ እየዋለ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የመደመር ትውልድ መፅሐፍ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመፅሐፉ ሽያጭ የቱሪዝም ስፍራዎችን እና የወጣቶች የመዝናኛ ስፍራዎችን ለመገንባት እንዲውል መወሰናቸውን ሀላፊዋ አውስተዋል።   ዓለም አቀፉ ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብም የመደመር ትውልድን በመገንባት ረገድ ሚናውን እንዲወጣ ጠይቀዋል። የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ መፅሐፉን በመግዛት በኢትዮጵያ የልማት ስራዎች ላይ አሻራውን እንዲያሳርፍ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ሀላፊዋ ጥሪ አቅርበዋል።   የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ መሆኑን የተናገሩት በመፅሐፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ ናቸው። የመደመር እሳቤ ዓለም አቀፋዊ መርሆን ያገናዘበ በመሆኑ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ እንደ የአውዱ ሊጠቀምበት እንደሚችልም ጠቁመዋል።
ኢትዮ-ቴሌኮም በአዲስ መልክ ያበለጸገውን ቴሌ ብር "ሱፐር አፕ"ይፋ አደረገ 
Mar 23, 2023 66
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) ፦ኢትዮ-ቴሌኮም በአዲስ መልክ ያበለጸገውን ቴሌ ብር "ሱፐር አፕ" የሞባይል መተግበሪያ ዛሬ ይፋ አደረገ። ተቋሙ የቴሌ-ብር አገልግሎት ባቀረበ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለትራንስፎርሜሽንና የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑ ተገልጿል። የማህበረሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በማቅለል ረገድም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱም እንዲሁ። በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረገው መተግበሪያም ከዚህ ቀደም ከነበረው መተግበሪያ ተጨማሪ አገልግሎቶች ተካተውበት በአዲስ መልኩ መበልጸጉ ተገልጿል። መተግበሪያው ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹና አስተማማኝ መሆኑም ተጠቅሷል። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ኩባንያው አገልግሎቱን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ መምጣቱን ተናግረዋል። ኩባንያው ዲጂታል ኢኮኖሚን እውን የማድረግ ሥራን አጠናክሮ በመቀጠል ኢትዮ-ቴሌኮም በዘርፉ የመሪነት ሚናውን እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። ኃብትን በአግባቡ ለመጠቀም በቴክኖሎጂ መታገዝ ወሳኝ መሆኑን ተናግረው ፤በዛሬው እለት ይፋ የሆነውም መተግበሪያ ይህንን ያሳልጣል ነው ያሉት። መተግበሪያው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ጥቅም ላይ የሚውሉ መተግበሪያዎች በአንድ የተካተቱበት መሆኑን ገልጸዋል። ጊዜንና ወጭን በመቆጠብ ረገድ መተግበሪያው ትልቅ ሚና እንዳለውም ጠቁመዋል። አገልግሎቱን ከፕሌይ ስቶር፣ ከአፕ ስቶርና ከአፕ ጋለሪ በማውረድ መጠቀም እንደሚቻል ተመላክቷል።
በግብርና ዘርፍ ሴቶችን ያማከለ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ እንደሆነ የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ
Mar 23, 2023 79
ባህር ዳር መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ በግብርና ዘርፍ ሴቶችን ያማከለ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ የኢኮኖሚ አቅማቸውን የሚያጠናክሩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በአማራ ክልል ሰሜን ሜጫ ወረዳ የሴቶችን የግብርና ተሳትፎ የሚያሳይ ጉብኝት ተካሄዷል። በጉብኝቱ የተሳተፉት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሶፊያ ካሳ እንዳሉት፤ ሴቶች በግብርናው መስክ በተገቢው መንገድ ከታገዙና ከተደገፉ ከኢኮኖሚ ጥገኝነት የሚላቀቁበት እድል ሰፊ ነው። ለዚህም ሴቶችን በግብርና ኤክስቴንሽን ተጠቃሚ በማድረግ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።   በተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ የግብዓት አቅርቦት፣ የሙያ እገዛ፣ የገበያ ትስስር መፍጠርና ሌሎች ድጋፎችን ሴቶች እንዲያገኙ አሰራር ተቀምጦ እየተተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ሴቶች ከተደገፉ የተሻለ ለውጥ እንደሚያስመዘግቡ በሰሜን ሜጫ ወረዳ በግብርና መስክ የተሰማሩ ሴቶች ያስመዘገቡት ውጤት ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፤ ድጋፉን ማሳደግ ላይ ቀሪ የቤት ስራዎች በትኩረት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። ይህን ለማጠናከር በአማራና ሲዳማ ክልል የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ተቀርፆ መተግበር መጀመሩን ጠቅሰው፤ ፕሮጀክቱ ሴቶችን በተለየ ሁኔታ የማብቃትና የማገዝ ስራ እያከናወነ እንደሆነ ጠቁመዋል።   የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የስርዓተ ፆታ ባለሙያ ወይዘሮ ማስተዋል ካሳሁን በበኩላቸው በክልሉ ሴቶች በግብርናው ዘርፍ ንቁ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው ብለዋል። በክልል ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን የሚበልጡ ሴቶችን በማካተት የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም በቀበሌ ደረጃ ጭምር ለሴቶች በቅርበት እገዛና ድጋፍ የሚያደርግ ባለሙያ ተመድቦ ሙያዊ እገዛ በመስጠት የግብርና ግብዓትና የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የሃብት አጠቃቀምና የስራ ክፍፍል እንዳይኖር ግንዛቤ እንዲያገኙ እየተደረገ ሲሆን በተሰራው ስራም ለውጥ እየመጣ መሆኑን አመልክተዋል።   በሰሜን ሜጫ ወረዳ በ9 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እየተከናወነ ባለው የበጋ ወራት የመስኖ ልማት እንቅስቃሴ 2 ሺህ 500 ሴቶች እየተሳተፉ ነው ያሉት ደግሞ የወረዳው ግብርና ፅህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ እስጢፋኖስ ስሜነህ ናቸው። ሴቶች የማዳበሪያና ምርጥ ዘር ግብዓት እጥረት እንዳይገጥማቸው በቀበሌ ባለሙያ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በሰሜን ሜጫ ወረዳ እናምርት ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ሴት አርሶ አደር መልሽው ሞላ እንዳሉት፤ በግብርና ባለሙያዎች በሚደረግላቸው ድጋፍ ቃሪያ፣ ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ አቮካዶና ስንዴ እያለሙ ነው። አሁን ካለሙት ጥቅል ጎመን ብቻ በመጀመሪያ ሽያጭ 13 ሺህ ብር ማግኘታቸውን ጠቅሰው፤ በጠቅላላ ካለሙትም ከ100 ሺህ ብር በላይ ገቢ እንደሚጠብቁ አስታውቀዋል። በጉብኝቱ ከፌደራል ግብርና ሚኒስቴርና ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተውጣጡ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ ነው - ዶክተር ምህረት ደበበ
Mar 23, 2023 112
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ ነው ሲሉ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ ተናገሩ።   "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ የእንግሊዝኛ ቅጂ የሆነው "Generation Medemer"ን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የማስተዋወቂያ መርሃ-ግብር በወዳጅነት ፓርክ ቁጥር ሁለት እየተካሄደ ነው።   የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ የመደመር ተከታታይ መጻሕፍት የያዟቸውን ፍልስፍናና የለውጥ እሳቤዎች ላይ ዳሰሳ አቅርበዋል። መደመር እሳቤ መሆኑን ጠቅሰው ጠቅላይ ሚኒስተሩ በመፅሃፋቸው የህይወት ተሞክሯቸውንም እንዳቀረቡ ነው ያነሱት። መደመር እያንዳንዱን ሃብት እውቀት ጉልበት እሳቤ ጊዜ አሰባስቦ ለለውጥና ለእድገት መጠቀምን ያሳያል ብለዋል።   የመደመር ትውልድ ፍቅርና መተባበር፣ ስሜትና አስተውሎት፣ መተማመንን የሚገነባ ማህበራዊ መሠረትን መገንባት፣ ልህቀትን መሻት መገለጫዎቹ ናቸው ብለዋል። መልካም ሥነ-ምግባር የመደመር ትውልድ ዋነኛ ባህሪ መሆኑን ተናግረው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመፅሐፋቸው የመደመር ትውልድ አምስተኛውና በተዋረዳዊ ቅብብሎሽ የመጣ መሆኑን አብራርተዋል ነው ያሉት። የዚህ ዓለም ትውልድ በመደመር እሳቤ መተባበርና ያለውን ሁለገብ አቅም ለጋራ ብልፅግና መጠቀም እንዳለበት የሚያትት ነው ብለዋል።   ያለንበት ዘመን ሉላዊነት፣ ጂኦ ፖለቲካ፣ ቴክኖሎጂ ያስተሳሰረው በመሆኑ የመደመር ትውልድም ከሀገር አልፎ ዓለም አቀፋዊነትን የሚያቀነቅን ሊሆን እንደሚገባው መጥቀሳቸውን አትተዋል። መደመር በአንድነት አገርን ወደ ከፍታ የማሻገር መንገድን የሚያሳይ መነፅር መሆኑን ጠቅሰዋል። የመደመር እሳቤ ዓለም አቀፋዊ መርሆን ያገናዘበ በመሆኑ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ እንደየአውዱ ሊጠቀምበት የሚችል ነው ብለዋል።
የአማራ ክልል ህብረት ስራ ማስፋፊያ ባለስልጣን በክልሉ የሰብል ምርት ዋጋን ለማረጋጋት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Mar 23, 2023 60
ባህር ዳር መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል እየናረ የመጣውን የሰብል ዋጋ ለማረጋጋት የሰብል ምርት በትስስር ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ህብረት ስራ ማስፋፊያ ባለስልጣን አስታወቀ። መርከብ ዩኒየን በባህር ዳር ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች 1ሺህ 700 ኩንታል የሰብል ምርት በቅናሽ ዋጋ ማሰራጨት ጀምሯል።   በዚህ ወቅት የባለስልጣኑ ሃላፊ አቶ ጌትነት አማረ እንደገለጹት፤ ህብረት ስራ ማህበራት 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በጀት መድበው የሰብል ምርት በመግዛት የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት እየሰሩ ይገኛሉ። እስካሁን ከ731ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ግዥ መፈፀሙን ጠቅሰው፤ ከዚህ ውስጥ 174ሺህ ኩንታል የሰብል ምርት በትስስር ለገበያ መረጋጋት እንዲውል መደረጉን ገልጸዋል። እየናረ የመጣውን የሰብል ምርት ዋጋ ለማረጋጋት ትርፍ አምራች በሆኑ አካባቢዎች የሚገኙ ዩኒየኖችና ህብረት ስራ ማህበራት በተመጣጣኝ ዋጋ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ የጋራ መግባባት ተፈጥሮ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ኢብራሂም መሀመድ በበኩላቸው፤ የህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች ገበያው እንዲረጋጋ የሰብል ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ህብረተሰብ እንዲያቀርቡ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ በባህር ዳር ከተማ የሚገኘው የመርከብ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበር ዩኒየን ባሳየው ቁርጠኝነት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጤፍ፣ በቆሎና የዳቦ ዱቄት ማቅረብ መጀመሩ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል። ሌሎች ዩኒየኖችና የህብረት ስራ ማህበራትም ይህንን አርአያነት ወስደው በየአካባቢያቸው ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ የሰብል ምርት በማቅረብ ዋጋውን ማረጋጋት እንዳለባቸው አመልክተዋል። ፋብሪካዎችም በቂ የስንዴ ምርት እንዲያገኙ ይሰራል ያሉት ዶክተር ኢብራሂም፤ የሸማች ህብረት ስራ ማህበራትም ምርቱን ለህብረተሰቡ በፍትሃዊነት ተደራሽ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። በቀጣይ አንድ ወር ውስጥ 10ሺህ ኩንታል የጤፍ፣ የበቆሎና የዳቦ ዱቄት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን የመርከብ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው እሸቱ አስታውቀዋል። ለባህር ዳር ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ የሚሆን አንድ ሺህ 700 ኩንታል ምርት በገበያ ከሚሸጠው ከ600 እስከ 1ሺህ ብር ቅናሽ ማከፋፈል ተጀምሯል ብለዋል። የልደታ ሸማቾች ህብረት ስራ ማህበር ሰብሳቢ ወይዘሮ ውብርስት እንዳለው፤ ከዩኒየኑ የተረከቡትን 40 ኩንታል የጤፍና የዳቦ ዱቄት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚያሰራጩ ተናግረዋል። በቀጣይም ማህበሩ በትስስር የሚያገኘውን ምርት በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ነዋሪዎች በፍትሃዊነት በማሰራጨት ገበያው እንዲረጋጋ የድርሻቸውን እንደሚወጣ ገልጸዋል።    
የሚታይ
የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የመደመር ትውልድን ግንባታ እንዲደግፍ ጥሪ ቀረበ
Mar 23, 2023 89
አዲስ አበባ መጋቢት 14/20115 (ኢዜአ)፦ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ባለው ተቋማዊ አቅም የመደመር ትውልድን ግንባታ እንዲደግፍ ጥሪ ቀረበ። አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ መደመር የኢትዮጵያን እምቅ አቅም በማሰባሰብ ሀገርን ወደ ከፍታ ለማሻገር በለውጡ የተወለደ የፖለቲካ ዕይታና ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰዋል።   መደመር ግቡ ያለፉ ጠባሳዎቻችንን ማከም፣ ችግርቻችንን በአገር በቀል እውቀት በጋራ መፍታት ነው ሲሉም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲሱ የመደመር ትውልድ መፅሃፋቸው የመደመር ትውልድ ከትናንት በመማር በጋራ ጥረታቸው ጠንካራዋንና የበለፀገች ኢትዮጵያን መገንባት እንዳለባቸው መክረዋል ብለዋል።   የጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በበኩላቸው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር እሳቤና የመደመር ትውልድ መጻህፍትን ሀገርና ዓለምን ለመጥ ቀም በማሰብ ለንባብ እንዳበቁ ተናግረዋል። መደመር ያለፉ ውስብስብ ሀገራዊ ችገሮችን በጋራ መፍታትን፣ ዓለም ቀፋዊ ትብብር ማጠናከርን የሚያስገነዘብ መሆኑንም ጠቅሰዋል።   ከመጻሕፍቱ ሽያጭ የሚገኘው ገንዘብ ለትውልዱ የሚጠቅሙ ፕሮጀክቶችን በማልማት ላይ እየዋለ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የመደመር ትውልድ መፅሐፍ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመፅሐፉ ሽያጭ የቱሪዝም ስፍራዎችን እና የወጣቶች የመዝናኛ ስፍራዎችን ለመገንባት እንዲውል መወሰናቸውን ሀላፊዋ አውስተዋል።   ዓለም አቀፉ ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብም የመደመር ትውልድን በመገንባት ረገድ ሚናውን እንዲወጣ ጠይቀዋል። የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ መፅሐፉን በመግዛት በኢትዮጵያ የልማት ስራዎች ላይ አሻራውን እንዲያሳርፍ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ሀላፊዋ ጥሪ አቅርበዋል።   የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ መሆኑን የተናገሩት በመፅሐፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ ናቸው። የመደመር እሳቤ ዓለም አቀፋዊ መርሆን ያገናዘበ በመሆኑ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ እንደ የአውዱ ሊጠቀምበት እንደሚችልም ጠቁመዋል።
የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ ነው - ዶክተር ምህረት ደበበ
Mar 23, 2023 112
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ ነው ሲሉ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ ተናገሩ።   "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ የእንግሊዝኛ ቅጂ የሆነው "Generation Medemer"ን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የማስተዋወቂያ መርሃ-ግብር በወዳጅነት ፓርክ ቁጥር ሁለት እየተካሄደ ነው።   የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ የመደመር ተከታታይ መጻሕፍት የያዟቸውን ፍልስፍናና የለውጥ እሳቤዎች ላይ ዳሰሳ አቅርበዋል። መደመር እሳቤ መሆኑን ጠቅሰው ጠቅላይ ሚኒስተሩ በመፅሃፋቸው የህይወት ተሞክሯቸውንም እንዳቀረቡ ነው ያነሱት። መደመር እያንዳንዱን ሃብት እውቀት ጉልበት እሳቤ ጊዜ አሰባስቦ ለለውጥና ለእድገት መጠቀምን ያሳያል ብለዋል።   የመደመር ትውልድ ፍቅርና መተባበር፣ ስሜትና አስተውሎት፣ መተማመንን የሚገነባ ማህበራዊ መሠረትን መገንባት፣ ልህቀትን መሻት መገለጫዎቹ ናቸው ብለዋል። መልካም ሥነ-ምግባር የመደመር ትውልድ ዋነኛ ባህሪ መሆኑን ተናግረው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመፅሐፋቸው የመደመር ትውልድ አምስተኛውና በተዋረዳዊ ቅብብሎሽ የመጣ መሆኑን አብራርተዋል ነው ያሉት። የዚህ ዓለም ትውልድ በመደመር እሳቤ መተባበርና ያለውን ሁለገብ አቅም ለጋራ ብልፅግና መጠቀም እንዳለበት የሚያትት ነው ብለዋል።   ያለንበት ዘመን ሉላዊነት፣ ጂኦ ፖለቲካ፣ ቴክኖሎጂ ያስተሳሰረው በመሆኑ የመደመር ትውልድም ከሀገር አልፎ ዓለም አቀፋዊነትን የሚያቀነቅን ሊሆን እንደሚገባው መጥቀሳቸውን አትተዋል። መደመር በአንድነት አገርን ወደ ከፍታ የማሻገር መንገድን የሚያሳይ መነፅር መሆኑን ጠቅሰዋል። የመደመር እሳቤ ዓለም አቀፋዊ መርሆን ያገናዘበ በመሆኑ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ እንደየአውዱ ሊጠቀምበት የሚችል ነው ብለዋል።
"የመደመር ትውልድ" መጽሐፍን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 23, 2023 65
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው። "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ የእንግሊዝኛ ቅጂ የሆነው "Generation Medemer"ን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር በወዳጅነት ፓርክ ቁጥር ሁለት ነው እየተካሄደ ያለው። በመርሐ -ግብሩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታዎች አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ እና አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም እንዲሁም መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም የመደመር ትውልድ የኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የመሻገር ህልሞች የሚያሳካ መሆኑን ከመፅሐፉ ጠቅሰው አቅርበዋል። መርሐ ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመጽሐፉ ምረቃ ላይ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች መደመር መጽሐፍን በመሸጥ ከሚገኘው ገቢ ለትውልዱ የሚጠቅሙ ፕሮጀክቶችን እንዲገነቡ ያቀረቡት ጥሪ አካል ነው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ምስጋኑ አርጋ በዚህ ወቅት፥ መደመር አዲስ ሀገርበቀል የፖለቲካ ለውጥ ዕሳቤ መሆኑን ጠቅሰዋል። የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሀገራዊ መግባባት ለማምጣት መፍትሔዎችን ያመላከተ ነው ብለዋል። አዲሱ የመደመር ትውልድ አቅሙን በማሰባሰብ ጠንካራዋን ኢትዮጵያን መገንባት እንዳለበት ተናግረዋል። የወጣቱን እምቅ እውቀትና ጉልበት ለሀገርና ለአህጉር ዕድገት መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።
የወተት ምርትን ለማሳደግ የዝርያ ማሻሻል፣ የመኖ አቅርቦትና የእንስሳት ማረፊያ ምቹነት ተቀናጅተው መተግበር አለባቸው - የዘርፉ ምሁራን
Mar 23, 2023 77
ሀዋሳ መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ የወተት ምርትን ለማሳደግ የዝርያ ማሻሻል፣ የመኖ አቅርቦትና የእንስሳት ማረፊያ ምቹነት ተቀናጅተው መተግበር እንዳለባቸው የዘርፉ ምሁራን አመለከቱ። የእንስሳት ምርታማነትን ለማሳደግ የተያዙ ዕቅዶች ስኬታማ እንዲሆኑ መንግስት፣ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ የምርምር ማዕከላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመስኩ ምሁራን አስገንዝበዋል።   በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ኮሌጅ በእንስሳት ሀብት ዙሪያ ምርምር እየሰሩ ያሉ ምሁራን ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ኢትዮጵያ ያላትን ከፍተኛ አቅም በመጠቀም ተጠቃሚ እንድትሆን በስፋት መሰራት አለበት። በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ስነ-ምግብ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አጀቡ ኑርፈታ የእንስሳት መኖ ሲዘጋጅ ምርት ለመስጠት የሚያስችሉ ንጥረ ነገሮችን መያዝ እንዳለበት አስገንዝበዋል። በመሆኑም የእንስሳቱ አመጋገብ ከእንስሳቱ የሚጠበቅን ምርት ሊሰጥ በሚያስችል መልኩ መሆን እንደሚገባው ገልጸው፤ የእንስሳት ዝርያ መረጣና የመኖ አቅርቦት ለውጤታማነት ቁልፍ ጉዳዮች እንደሆኑ ገልጸዋል። የመኖ ዝግጅት ከመጀመሪያ ጀምሮ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የገለጹት ፕሮፌሰር አጀቡ፤ የአርሶ አደሩን ህይወት ለመቀየርና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲም የእንስሳት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻዎች ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   በእንስሳትና ተፈጥሮ ግጦሽ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ በእንስሳት እርባታና ጄኔቲክስ ዘርፍ ፕሮፌሰር አበራ መለሰ በበኩላቸው እንዳሉት በዶሮ ስጋና እንቁላል ምርታማነት ላይ በዋናነት የተለያዩ ምርምሮችን ሲያደርጉ ቆይተዋል። የዶሮና እንቁላል ምርታማነትን በማሳደግ እያንዳንዱ ቤተሰብ በአነስተኛ የዶሮ እርባታ ተሳትፎ እንዲኖረው በምርምር የማገዝ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   የእንስሳት መኖ ላይ የተደረጉ የምርምር ስራዎች ውጤት እንደታየባቸው አመልክተው፤ ከዶሮ መኖ ጋር በተያያዘ በሞሪንጋ /ሽፈራው/ ተክል ላይ ያደረጉት ምርምር በመኖነት ለዶሮዎች ቢቀርብ የእንቁላል ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚያስችል መረጋገጡን ጠቁመዋል።   በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ትምህርት ክፍል ዳይሬክተር በእንስሳትና ግጦሽ ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህር፣ ተማራማሪና በወተት ዘርፍ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ስንታየሁ ይግረም በበኩላቸው በቀን እስከ 30 ሊትር ወተት የመስጠት አቅም ያላቸው ላሞች በአያያዝ ችግር ከስድስት ሊትር በላይ እንዳይሰጡ ማድረጉን ጠቁመዋል። ይህን ችግር መፍታት የሚቻለው በተገቢው መንገድ እንስሳቱን መያዝና የተመጣጠነ መኖ በማቅረብ ሲሰራ ነው በማለት ገልጸው፤ ከዝርያ በተጨማሪ የመኖና የእንስሳት ማረፊያ ትኩረት እንደሚያስፈልጋቸው ገልጸዋል።   የእንስሳትን ምርታማነት የማሳደግ ስራ የዝርያ ማሻሻል፣ የመኖ አቅርቦትና የእንስሳት ማረፊያ ምቹነት ተቀናጅተው መተግበር እንዳለባቸው ያስገነዘቡት ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ስንታየሁ፤ በተናጠል የሚካሄደው ስራ ውጤት እንደማያመጣ ገልጸዋል።   በመሆኑም ዝርያ ማሻሻል፣ በቂ መኖና ውሀ ማቅረብ፣ ለእንስሳት ማረፊያ ምቹ ስፍራ ማዘጋጀት ለምርታማነት ማደግ ቁልፍ ጉዳዮች በመሆናቸው ተቀናጅተው መተግበር እንዳለባቸው አስረድተዋል። እነዚህን ተግባራት በተገቢው መንገድ በመከተል የተሟላ ውጤት ማምጣት የሚያስችል ሙሉ ፓኬጅ መጠቀም እንደሚገባ ገልጸዋል።
የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ፖሊሲ ቀርጾ የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ የመንግሥት ትኩረት ነው - የፕላንና ልማት ሚኒስቴር
Mar 23, 2023 81
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦ የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ፖሊሲ ቀርጾ ለዜጎች የተሟላ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽ ማድረግ የመንግሥት የአሥር ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ አንዱ አካል መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በህፃናት የአመጋገብ ሥርዓት፣ የህፃናት መቀንጨር ያለበትን ደረጃ፣ የሚያጠቡና ነፍሰ-ጡር እናቶች ጤናማ አመጋገብ ላይ ትኩረት ያደረገ የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ስትራቴጂ ዳሰሳ ጥናት ይፋ ሆኗል፡፡   በዳሰሳ ጥናቱ መሰረት በኢትዮጵያ የህፃናት ደጋግሞ የመመገብና የተመጣጠነ ምግብ የማግኘት ዕድል ከክልል ክልል የተለያየ ቢሆንም በጥቅሉ ዝቅተኛ ነው፡፡ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ፤ መንግሥት በአሥር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ ትኩረት ከሰጣቸው ተግባራት መካከል አንዱ ሥርዓተ-ምግብን ማሻሻል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ምግብና ሥርዓተ-ምግብን ለማረጋገጥ ከምርት እስከ አመጋገብ ባህል ባለው ሂደት በርካታ ተዋንያን የሚሳተፉበት በመሆኑ ተጠያቂነትን ያካተተ የጋራ ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በአሥር ዓመት መሪ የልማት ዕቅዱ ትልቅ ቦታ የተሰጠው የሰው ኃይል ልማት መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ ብቁ የሰው ኃይል ማዘጋጀት የሚቻለው ጤናማ ዜጋ ማፍራት ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደ ሀገር የሥርዓተ-ምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ ግልጽ የሆነ ፖሊሲ ማስፈጸም የሚያስችሉ ስትራቴጂዎችና ፕሮግራሞች ተቀርጸው ትግበራ ላይ መሆናቸውንም አብራርተዋል፡፡   የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ እንዳሉት፤ የሕዝቦችን ጤና እና ጤንነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ ምርምሮች ይደረጋሉ፡፡ በእናቶችና ህፃናት የአመጋገብ ሥርዓት ላይ የሚያተኩረው የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ስትራቴጂ የዳሰሳ ጥናትም የዚሁ አካል መሆኑን ገልጸዋል፡፡   በተባበሩት መንግሥታት የህፃናት መርጃ ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ዶክተር አቡበከር ካምፖ፤ ኢትዮጵያ የምግብና ሥርዓተ-ምግብን ለማሻሻል የምታደርገው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡ ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ የማስፈጸሚያ ስትራቴጂዎች፣ ደንቦችና አሰራሮችን ማውጣት የመንግሥትን ቁርጠኝነት ማሳያዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የምግብ እጥረት ችግርን ለማቃለል እየተደረገ ባለው ጥረት ተጨባጭ ለውጥ እየታየ መሆኑንም ተናግረዋል።
ማስታወቂያ
ፖለቲካ
"የመደመር ትውልድ" መጽሐፍን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 23, 2023 65
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው። "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ የእንግሊዝኛ ቅጂ የሆነው "Generation Medemer"ን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር በወዳጅነት ፓርክ ቁጥር ሁለት ነው እየተካሄደ ያለው። በመርሐ -ግብሩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታዎች አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ እና አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም እንዲሁም መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም የመደመር ትውልድ የኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የመሻገር ህልሞች የሚያሳካ መሆኑን ከመፅሐፉ ጠቅሰው አቅርበዋል። መርሐ ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመጽሐፉ ምረቃ ላይ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች መደመር መጽሐፍን በመሸጥ ከሚገኘው ገቢ ለትውልዱ የሚጠቅሙ ፕሮጀክቶችን እንዲገነቡ ያቀረቡት ጥሪ አካል ነው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ምስጋኑ አርጋ በዚህ ወቅት፥ መደመር አዲስ ሀገርበቀል የፖለቲካ ለውጥ ዕሳቤ መሆኑን ጠቅሰዋል። የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሀገራዊ መግባባት ለማምጣት መፍትሔዎችን ያመላከተ ነው ብለዋል። አዲሱ የመደመር ትውልድ አቅሙን በማሰባሰብ ጠንካራዋን ኢትዮጵያን መገንባት እንዳለበት ተናግረዋል። የወጣቱን እምቅ እውቀትና ጉልበት ለሀገርና ለአህጉር ዕድገት መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።
የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ የተፋሰሱን አገራት መተማመን የሚሸረሽር ነው-ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ
Mar 23, 2023 89
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሚመለከት የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ የመርህ ስምምነቱን የጣሰና የተፋሰሱን አገራት መተማመን የሚሸረሽር መሆኑን የዓባይ ውኃ ጉዳይ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ገለጹ። የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር “ሁሉም አማራጮች ክፍት ናቸው” በሚል ግድቡን አስመልክቶ መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የግብጽ መግለጫ ኃላፊነት የጎደለው እና ተቀባይነት የሌለው ሲል ተናግሯል። መግለጫው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተርና የአፍሪካ ሕብረት የመተዳደሪያ ደንብን የጣሰ ስለመሆኑም አመላክቷል። ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን እ.ኤ.አ በ2015 የተፈራረሙትን የመርሆዎች ስምምነት በግልጽ የጣሰ መግለጫ ሆኗል። በጉዳዩ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና የዓባይ ውኃ ጉዳይ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ፤ በግብጽ በኩል የወጣው መግለጫ የአረብ ሊግን ድጋፍ ለማግኘት ያለመ መሆኑን ይገልጻሉ። የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሳሚ ሹክሪ፤ የአረብ ሊግ የሕዳሴ ግድብን እንዲቃወምና ከግብጽ ጎን እንዲቆም በማለት በሊጉ ጉባዔ ላይ አንስተዋል። ከዚህም ባለፈ ሚኒስቴሩ “ሁሉም አማራጮች ክፍት ናቸው” በሚል ሕዳሴ ግድብን በሚመለከት ያወጣው መግለጫ የመርህ ስምምነቱን የጣሰና የተፋሰሱን አገራት መተማመን የሚሸረሽር መሆኑን ፕሮፌሰር ያዕቆብ አብራርተዋል።። ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የውኃ ሙሌት እያከናወነች ያለው ኃላፊነት በተሞላበትና የታችኞቹን የተፋሰሱ አገራት በማይጎዳ መልኩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ልማቱም የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በግድቡ ዙሪያ በግብጽ በኩል የወጣው መግለጫ ኃላፊነት የጎደለው ቢሆንም ኢትዮጵያ በአስተውሎት ምላሽ መስጠቷን ፕሮፌሰር ያዕቆብ አድንቀዋል። በኢትዮጵያዊያን የጋራ ጥረት እየተገነባ ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ወደ ኃይል ማመንጨት መሸጋገሩ ይታወቃል። በመሆኑም በግብጽ መንግሥት በኩል የሚወጡ አደናጋሪ መግለጫዎችን በመተው የግድቡን ግንባታ ለማጠናቀቅ ኢትዮጵያዊያን ሁለንተናዊ ድጋፋቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ነው ያሉት። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት አደራዳሪነት መፍትሔ እንደሚመጣ በማመን የሦስትዮሽ ድርድሩ ሁሉንም አሸናፊ ባደረገ መልኩ እንዲቋጭ አሁንም ቁርጠኛ መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጹ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሀገር ገፅታ ግንባታና በለውጥ ስራዎች እያከናወናቸው ያለውን ተግባራት አጠናክሮ ሊያስቀጥል ይገባል- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
Mar 23, 2023 82
አዳማ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሀገር ገፅታ ግንባታና በለውጥ ስራዎች ረገድ እያከናወናቸው ያለውን ተግባራት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስገነዘበ። የምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮችና አባላት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን የለውጥ ስራዎች እንቅስቃሴና የአሰራር ማሻሻያዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በአዳማ ተካሄዷል።   የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ እውነቱ አለነ በዚሁ ወቅት፤ ኢዜአ አበረታች የለውጥ፣ የአሰራርና የይዘት ስራዎች ማሻሻያ እያከናወነ መሆኑን መገንዘባቸውን ተናግረዋል። እነዚህ የለውጥ ስራዎች "ተቋሙን አሁን ካለበት ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚወስዱ ናቸው" ያሉት ሰብሳቢው፤ በቀጣይም ተወዳዳሪነቱንና ታማኝ የዜና ምንጭነቱን በዘላቂነት ለማስቀጠል በቴክኖሎጂና በሰው ኃብት ልማት ማስደገፍ ይገባዋል ነው ያሉት።   ለዚሁ ማጠናከሪያም እየተገበራቸው ያሉትን የሪፎርም ስራዎች አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። ቋሚ ኮሚቴው ተቋሙን በቀጣይነት ለመደገፍ፣ ለማገዝና ለመከታተል አጋዥ የሆኑ ግብዓቶችና ያለበትን የለውጥ ምዕራፍ የተመለከተ መረጃ ማግኘቱንም ገልጸዋል።   ተቋሙ የሁሉም ሚዲያዎች መጋቢና መሪ እንደመሆኑ አሁን ካለበት በላይ ብቁ የሰው ሃይል፣ በቴክኖሎጂና በፋይናንስ አቅም ራሱን ለማጠናከር መስራት እንደሚገባው አመላክተዋል። በተቋሙ እየተዘጋጀ ያለውን አዲስ የሰራተኞች መተዳደሪያ ረቂቅ ደንብ በግብዓት ለማዳበር የሚያስችል ግንዛቤ መፈጠሩን ጠቅሰዋል።   የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው መድረኩ ኢዜአ ያለበትን ጉድለት እየፈተሸ ተልእኮውን እንዲያሳካ ገንቢ ግብዓት የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። "ኢዜአ ራሱን መመልከት ያለበት ከዓለም አቀፍ አቻ ተቋማት ጋር ነው" ያሉት አቶ ሰይፈ፤ በተለይም በሀገር ገፅታ ግንባታ ላይ የሚጠበቅበትን ሚና መወጣት የሚያስችለውን አቅም ለመፍጠርና ተወዳዳሪ ለመሆን እየሰራ ነው ብለዋል።   ተቋሙ ህጎችና አሰራሮችን ከማሻሻል ጀምሮ ዘርፈ ብዙ የለውጥ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የተናገሩት አቶ ሰይፈ፤ በተለይም ተልዕኮውን ለማሳካት የሚያስችለውን አቅም ለመፍጠር ከሀገር ውስጥና ከውጭ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በሰው ሃይል አቅም ግንባታና ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።
ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ ትብብር አጠናክራ ትቀጥላለች - አምባሳደር ጃኦ ጂዩዋን
Mar 23, 2023 115
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ጃኦ ጂዩዋን ገለጹ። በቅርቡ በኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት ልዑክ በቻይና ያደረገው ይፋዊ የስራ ጉብኝት የአገራቱን ግንኙነት በማጠናከር በኩል ትልቅ ድርሻ አለው ብለዋል። ልዑኩ በቆይታው ከቻይና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ጋር የሁለቱ አገራት ግንኙነት ሊጠናከር በሚችልባቸው በርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን ነው የተናገሩት። የንግድና ኢንቨስትመንት፣ የመሰረተ-ልማት ግንባታ ግንኙነቱን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ምክክር መደረጉን ጠቅሰው የብድር ማስተካከያ አስፈላጊነትን በተመለከተም የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል። የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በጤና፣ በኃይል ልማትና በማዕድን ዘርፍ ተሳትፏቸው የበለጠ እንዲጠናከር የማበረታታት ሥራው እንደሚቀጥል ማረጋገጫ ተሰጥቷል ብለዋል። በተጨማሪም የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ ትብብሩን ማሳለጥ የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ እንዲዋቀር ሥምምነት ላይ መደረሱንም አንስተዋል። እያደገ የመጣውን የሁለቱ አገራት የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ አምባሳደሩ አረጋግጠዋል። ዘንድሮ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ሥራዎችን ለማከናወን ቻይና የቀረጸችው "የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ" 10ኛ ዓመቱን እንደሚይዝ ገልጸው ኢትዮጵያ በእነዚህ ዓመታት ጠንካራ ግንኙነት እንደነበራት አስታውሰዋል። በቀጣይም በኢኒሼቲቩ ማዕቀፍ በኢትዮጵያ የሚካሄዱ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎችን ለማሳለጥና ትበብሩን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰራ ገልጸዋል። በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን አጋርነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመው በተለይም የኢትዮጵያ ተማሪዎች በቻይና በዘርፉ የሚሰጣቸውን የሥልጠና እድል ለማስፋት ትኩረት ተደርጓል ብለዋል። የቻይና ሥመ-ጥር የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ሥራ ተሳትፏቸውን ለማጠናከር እንደሚሰራም ገልጸዋል። በሌላ በኩል በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተከስቶ የነበረው ጦርነት በሰላም ሥምምነት መቋጨቱን ቻይና በአድናቆት እንደምትመለከተው ገልጸው ሥምምነቱ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ሰላም ለአፍሪካ ቀንድና ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም ወሳኝ ነው ያሉት አምባሳደር ጃኦ ጂዩዋን ሥምምነቱ ይህንን በማረጋገጥና ኢትዮጵያን ወደ ቀድሞ ሰላምና የአኮኖሚ ግንባታ ሥራ ለመመለስ አበርክቶው ከፍተኛ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባትና ለችግር ለተጋለጡ ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ ለማቅረብ የሚያደርገውን ጥረት በመደገፍ ቻይና ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን ትቆማለች ነው ያሉት። የመልሶ ግንባታ ሥራው ከተጠናቀቀ በኋላ የቻይና ባለሃብቶች በእነዚህ አካባቢዎች በኢንቨስትመንት ሥራ እንዲሰማሩ ለማድረግም ጥረት ይደረጋል ብለዋል። ቻይና የዓለምን ሰላም ለማረጋገጥ ባለፈው ዓመት ያወጣችውን "ዓለም አቀፍ የደኅንነት ኢኒሼቲቭ" መሰረት በማድረግ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በመተባበር በአፍሪካ ቀንድና በምስራቅ አፍሪካ ሰላምና መረጋጋት ለማጽናት በቅንጅት እንደምትሰራ ተናግረዋል። እንደ አወሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2022 በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ 2 ነጥብ 19 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን በኢትዮጵያ የቻይና ቀጥታ ኢንቨስትመንትም 3 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። የኢትዮጵያና የቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1970 ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳድር አድርገው ሾሙ
Mar 23, 2023 222
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳድር አድርገው ሾመዋል። የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 62 (9) እና በአዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀፅ 14/2/ለ/ መሠረት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት፤ እንዲሁም በኢፌዴሪ መንግሥት እና በህወሓት መካከል ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እና ግጭትን ለማቆም በፕሪቶርያ ደቡብ አፍሪካ በተደረገው የሰላም ስምምነት አንቀጽ 10(1) መሠረት አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም በማስፈለጉ፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በመጋቢት 9/2015 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ “የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር ደንብን አፅድቋል። በዚሁ ደንብ አንቀጽ 3(2) መሠረት የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳድር አድርገው ሾመዋል። ርዕሰ መስተዳደሩ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎችን ውክልና የሚያረጋገጥ እና አካታች የሆነ አስተዳደር በማዋቀር የክልሉን አስፈፃሚ አካል የመምራት እና የማስተባበር ኃላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
አስፈጻሚው አካል ሀላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ ምክር ቤቱ የተጠናከረ ቁጥጥርና ክትትል እያደረገ ነው---ቋሚ ኮሜቴዎች 
Mar 22, 2023 110
ሀዋሳ መጋቢት 13/2015 (ኢዜአ) አስፈጻሚው አካል ሀላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ ምክር ቤቱ የቁጥጥርና ክትትል ሥራ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ገለጹ። ሰብሳቢዎቹ በምክር ቤቱ የሚወጡ ህጎች፣ አዋጆችና ደንቦች በትክክል ሥራ ላይ መዋላቸውን በመገምገም ክፍተት ሲኖርም ፈጥኖ እንዲታረም የማድረግ ሥራ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ ሙስናና ብልሹ አሰራሮች እንዲታረሙ ትኩረት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በሲዳማ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ህጻናት፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ አየለች ሌዳሞ እንዳሉት፣ አስፈጻሚው አካል የተጣለበትን ሀላፊነት በአግባቡ እንዲወጣ ኮሚቴው አስፈላጊውን ክትትልና ቁጥጥር ያደርጋል። "በእዚህም ቋሚ ኮሚቴው የሚከናወኑ ጉዳዮችን በመገምገም ያሉትን ጥንካሬዎችና ጉድለቶች ለይቶ ግብረ መልስ ይሰጣል" ያሉት ሰብሳቢዋ፣ በተሰጠው ግብረ መልስ መሰረት ጉድለቶች መታረማቸውን ክትትል እንደሚደረገም አስታውቀዋል። በሴቶችና ሕጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ከመከላከል አንጻር ለሚመለከታቸው አስፈጻሚ አካላት ተገቢ ድጋፍ በማድረግ ጥቃቶችን ቀድሞ ከማስቆም አንጻር ጥሩ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ከሴቶች ተጠቃሚነት አንጻር በክልሉ ጥሩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን በተደረገው ክትትል መረጋገጡን የገለጹት ወይዘሮ አየለች፣ "በአሰራር የገጠሙ ጉድለቶች እንዲታረሙ በቋሚ ኮሚቴው በኩል በቂ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ነው" ብለዋል። ሰብሳቢዋ እንዳሉት ከአገልግሎት አሰጣጥና ሙስና ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመገምገምና አስተያየት በመስጠት የህዝቡ ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝም በትኩረት እየተሰራ ነው። በምክር ቤቱ የህግ፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዮሴፍ ዮሳ በበኩላቸው እንዳሉት የምክር ቤቱ አባላትና ቋሚ ኮሚቴው አስፈጻሚውን አካል ከመከታተል፣ ከመቆጣጠርና ከመደገፍ በተጨማሪ የወጡ ህጎች በአግባቡ ሥራ ላይ መዋላቸውን ይከታተላሉ። በክልሉ ምክር ቤት የተለያዩ አዋጆች እንደሚወጡ ያስታወሱት አቶ ዮሴፍ "ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በትክክል ሥራ ላይ ውለው ያመጡትን ለውጥ ክትትል ይደረጋል" ብለዋል። በዚህ በኩል በክልሉ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ መልካም የሚባል መሆኑን ገልጸው፣ ኮሚቴው የተሰጠውን ሃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት ያደረጋቸው የክትትል ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልቅ ስጋት እየሆነ የመጣውን ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ የምክር ቤቱ አባላት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የክልል ጥያቄን ተከትሎ በነበረው የሽግግር ጊዜ ግርግሩን ተጠቅሞ የተሰሩ የሙስና ወንጀሎች እንዳሉ የተናገሩት አቶ ዮሴፍ፣ ይህን በተገቢው መንገድ ተከታትሎ ለማረምና የተመዘበረ ሀብት ለማስመለስ ምክር ቤቱ በትኩረት መስራቱንም አመልክተዋል። በእዚህም ባለፉት ሰባት ወራት ከምዝበራ ጋር በተያያዘ በተደረገ የኦዲት ግኝት 21 ሚሊዮን ብር ተመላሽ መደረጉንም አቶ ዮሴፍ ገልጸዋል። "ከዚህ ባለፈ 100 የሚሆኑ አመራሮች፣ የስራ ሀላፊዎች እና ሠራተኞች በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል" ብለዋል። የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚጎዱ ተግባራት ተጠያቂነት ባሰፈነ መልኩ በአግባቡ እንዲታረሙ ምክር ቤቱ የሚያደርገው ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር ሁለተኛ የስራ ዘመን አራተኛ መደበኛ ጉባዔ በሃዋሳ ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሕወሓት ላይ አሳልፎ የነበረውን የሽብርተኝነት ውሳኔ አነሳ
Mar 22, 2023 172
አዲስ አበባ መጋቢት 13/2015 (ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ላይ አሳልፎ የነበረውን የሽብርተኝነት ውሳኔ አነሳ። የሕወሓት ከአሸባሪነት መነሳት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በፌደራል መንግሥትና በሕወሓት መካከል የተደረሰውን የሠላም ሥምምነት ተግባራዊነት ለማፋጠን ይረዳልም ተብሏል። በምክር ቤቱ የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ ሕወሓት ከአሸባሪነት መዝገብ እንዲነሳ ያስፈለገበትን ምክንያት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ በአገሪቷ ዘላቂ ሰላም እየሰፈነ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ይህም ለኢትዮጵያ ህዝብ እፎይታ የሰጠ ነው ብለዋል፡፡ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ህወሓት ሲከተለው ከነበረው ኢህገ-መንግስታዊ እና በሽብር እንዲፈረጅ ያደረጉትን ተግባራት እያሻሻለ መምጣቱንም ጠቁመዋል፡፡   በሰላም ስምምነቱ ወቅት መግባባት ላይ የተደረሱባቸው ነጥቦችም ፍሬ ማፍራት መጀመራቸውን የተናገሩት አቶ ተስፋዬ በልጂጌ፤ ስምምነቱን በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ምክር ቤቱ ከዚህ ቀደም በሕወሓት ላይ አሳልፎ የነበረውን የአሸባሪነት ውሳኔ እንዲያነሳ ጠይቀዋል፡፡ ይህም እንደ አገር ዘላቂ ሰላምን ለመገንባትና ልዩነቶችን በሰለጠነ መልኩ ለመፍታት አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ምክር ቤቱም ከዚህ ቀደም አሳልፎት የነበረውን የአሸባሪነት ውሳኔ በማንሳት የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲደረግ የበኩሉን እንዲወጣ የውሳኔ ሃሳብ አቅርበዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የምክር ቤቱ አባላት፤ ኢትዮጵያ ወደ ዘላቂ ሰላም እንድታመራ ከዚህ ቀደም ተላልፎ የነበረው ውሳኔ መነሳቱ ተገቢ ነው ብለዋል፡፡ ይህም የሰላም ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግና የተጀመረውን የሰላም ሂደት ለማጽናት ያግዛል ነው ያሉት፡፡ የውሳኔ ሃሳቡን በመቃወም አስተያየታቸውን የሰጡ የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው በሰላም ስምምነቱ መሰረት ሕወሓት ትጥቅ ባልፈታበት ሁኔታ ከአሸባሪነት መዝገብ ማንሳት በአገር ላይ አደጋ ሊፈጥር እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ሕወሃት ከአሸባሪነት መዝገብ ከመነሳቱ በፊት የሰላም ስምምነቱ አተገባባር ለምክር ቤቱ ቀርቦ መገምገም እንዳለበት አንስተው፤ የውሳኔ ሃሳቡን ተቃውመዋል፡፡   የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በምላሻቸውም ህወሃትን ከአሸባሪነት መዝገብ ማንሳት የሰላም ስምምነቱን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም፣ ስምምነቱን ሳይሸራረፍ ተግባራዊ ለማድረግ እና የተጀመረውን የሰላም ሂደት ለማጽናት ትልቅ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በሰላም ስምምነቱ መሰረት የሕወሓት ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታት ሂደት ከከባድ መሳሪያዎች መጀመሩን ጠቅሰው፤ ሕወሃትን ከአሸባሪነት መዝገብ ማንሳት ይህን ስራ ለማጠናከር እንደሚያግዝ አመልክተዋል። በመሆኑም የምክር ቤቱ አባላት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ እንዲያጸድቁ ጠይቀዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በውሳኔ ሃሳቡ ላይ ጥልቅ ውይይት ካደረጉ በኋላ በአብላጫ ድምጽ አጽድቀዋል፡፡፡    
ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት አገርን ለመገንባት  ለጸረ ሙስና ትግሉ ውጤታማነት ሁሉም  ኃላፊነቱን  ሊወጣ ይገባል
Mar 22, 2023 118
አዲስ አበባ መጋቢት 13/2015 (ኢዜአ) ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት አገርን ለመገንባት ለጸረ ሙስና ትግሉ ውጤታማነት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ የፌደራል ሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ በፌዴራል ተቋማት ስር ለሚገኙ ለስነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ክፍል፣ ለውስጥ ኦዲት አገልግሎት፣ለሕግ አገልግሎት እና ለተቋማት ለውጥ ስራ አመራር ኃላፊዎች ያዘጋጀው ስልጠና ዛሬ በቢሾፍቱ ተጀምራል። በስልጠናው የዩኒቨርስቲዎች ሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ክፍል ኃላፊዎችም ተሳትፈዋል። የፌደራል ሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወዶ አጦ ሙስና ኢትዮጵያ ከተጋረጡባት ዋንኛ ችግሮች መካከል አንዱ መሆኑንና እየቀያየረ ያለው ሙስና የኢኮኖሚ እድገትን በመግታት ፣አንድነትን በማናጋት ስርዓተ መንግስቱን ለመናድ አደጋ የሚጋርጥ መሆኑን ገልጸዋል ። ችግሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የደህንነት ስጋት በመሆኑ መንግስት ሙስናን ለመታገል ብሔራዊ ኮሚቴ አዋቅሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ጠንካራ ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት አገር ለመገንባት የተጀመረው የፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል። ሁሉም የፀረ-ሙስና ትግሉ ባለቤት መሆን እንዳለበትም ነው ምክትል ኮሚሽነሩ ያመለከቱት። ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ከ260 በላይ የፌደራል ተቋማት የስራ ኃላፊዎች መሳተፋቸው ተገልጿል።
ፖለቲካ
"የመደመር ትውልድ" መጽሐፍን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 23, 2023 65
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው። "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ የእንግሊዝኛ ቅጂ የሆነው "Generation Medemer"ን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር በወዳጅነት ፓርክ ቁጥር ሁለት ነው እየተካሄደ ያለው። በመርሐ -ግብሩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታዎች አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ እና አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም እንዲሁም መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም የመደመር ትውልድ የኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የመሻገር ህልሞች የሚያሳካ መሆኑን ከመፅሐፉ ጠቅሰው አቅርበዋል። መርሐ ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመጽሐፉ ምረቃ ላይ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች መደመር መጽሐፍን በመሸጥ ከሚገኘው ገቢ ለትውልዱ የሚጠቅሙ ፕሮጀክቶችን እንዲገነቡ ያቀረቡት ጥሪ አካል ነው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ምስጋኑ አርጋ በዚህ ወቅት፥ መደመር አዲስ ሀገርበቀል የፖለቲካ ለውጥ ዕሳቤ መሆኑን ጠቅሰዋል። የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሀገራዊ መግባባት ለማምጣት መፍትሔዎችን ያመላከተ ነው ብለዋል። አዲሱ የመደመር ትውልድ አቅሙን በማሰባሰብ ጠንካራዋን ኢትዮጵያን መገንባት እንዳለበት ተናግረዋል። የወጣቱን እምቅ እውቀትና ጉልበት ለሀገርና ለአህጉር ዕድገት መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።
የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ የተፋሰሱን አገራት መተማመን የሚሸረሽር ነው-ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ
Mar 23, 2023 89
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሚመለከት የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ የመርህ ስምምነቱን የጣሰና የተፋሰሱን አገራት መተማመን የሚሸረሽር መሆኑን የዓባይ ውኃ ጉዳይ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ገለጹ። የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር “ሁሉም አማራጮች ክፍት ናቸው” በሚል ግድቡን አስመልክቶ መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የግብጽ መግለጫ ኃላፊነት የጎደለው እና ተቀባይነት የሌለው ሲል ተናግሯል። መግለጫው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተርና የአፍሪካ ሕብረት የመተዳደሪያ ደንብን የጣሰ ስለመሆኑም አመላክቷል። ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን እ.ኤ.አ በ2015 የተፈራረሙትን የመርሆዎች ስምምነት በግልጽ የጣሰ መግለጫ ሆኗል። በጉዳዩ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና የዓባይ ውኃ ጉዳይ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ፤ በግብጽ በኩል የወጣው መግለጫ የአረብ ሊግን ድጋፍ ለማግኘት ያለመ መሆኑን ይገልጻሉ። የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሳሚ ሹክሪ፤ የአረብ ሊግ የሕዳሴ ግድብን እንዲቃወምና ከግብጽ ጎን እንዲቆም በማለት በሊጉ ጉባዔ ላይ አንስተዋል። ከዚህም ባለፈ ሚኒስቴሩ “ሁሉም አማራጮች ክፍት ናቸው” በሚል ሕዳሴ ግድብን በሚመለከት ያወጣው መግለጫ የመርህ ስምምነቱን የጣሰና የተፋሰሱን አገራት መተማመን የሚሸረሽር መሆኑን ፕሮፌሰር ያዕቆብ አብራርተዋል።። ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የውኃ ሙሌት እያከናወነች ያለው ኃላፊነት በተሞላበትና የታችኞቹን የተፋሰሱ አገራት በማይጎዳ መልኩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ልማቱም የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በግድቡ ዙሪያ በግብጽ በኩል የወጣው መግለጫ ኃላፊነት የጎደለው ቢሆንም ኢትዮጵያ በአስተውሎት ምላሽ መስጠቷን ፕሮፌሰር ያዕቆብ አድንቀዋል። በኢትዮጵያዊያን የጋራ ጥረት እየተገነባ ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ወደ ኃይል ማመንጨት መሸጋገሩ ይታወቃል። በመሆኑም በግብጽ መንግሥት በኩል የሚወጡ አደናጋሪ መግለጫዎችን በመተው የግድቡን ግንባታ ለማጠናቀቅ ኢትዮጵያዊያን ሁለንተናዊ ድጋፋቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ነው ያሉት። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት አደራዳሪነት መፍትሔ እንደሚመጣ በማመን የሦስትዮሽ ድርድሩ ሁሉንም አሸናፊ ባደረገ መልኩ እንዲቋጭ አሁንም ቁርጠኛ መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጹ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሀገር ገፅታ ግንባታና በለውጥ ስራዎች እያከናወናቸው ያለውን ተግባራት አጠናክሮ ሊያስቀጥል ይገባል- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
Mar 23, 2023 82
አዳማ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሀገር ገፅታ ግንባታና በለውጥ ስራዎች ረገድ እያከናወናቸው ያለውን ተግባራት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስገነዘበ። የምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮችና አባላት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን የለውጥ ስራዎች እንቅስቃሴና የአሰራር ማሻሻያዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በአዳማ ተካሄዷል።   የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ እውነቱ አለነ በዚሁ ወቅት፤ ኢዜአ አበረታች የለውጥ፣ የአሰራርና የይዘት ስራዎች ማሻሻያ እያከናወነ መሆኑን መገንዘባቸውን ተናግረዋል። እነዚህ የለውጥ ስራዎች "ተቋሙን አሁን ካለበት ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚወስዱ ናቸው" ያሉት ሰብሳቢው፤ በቀጣይም ተወዳዳሪነቱንና ታማኝ የዜና ምንጭነቱን በዘላቂነት ለማስቀጠል በቴክኖሎጂና በሰው ኃብት ልማት ማስደገፍ ይገባዋል ነው ያሉት።   ለዚሁ ማጠናከሪያም እየተገበራቸው ያሉትን የሪፎርም ስራዎች አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። ቋሚ ኮሚቴው ተቋሙን በቀጣይነት ለመደገፍ፣ ለማገዝና ለመከታተል አጋዥ የሆኑ ግብዓቶችና ያለበትን የለውጥ ምዕራፍ የተመለከተ መረጃ ማግኘቱንም ገልጸዋል።   ተቋሙ የሁሉም ሚዲያዎች መጋቢና መሪ እንደመሆኑ አሁን ካለበት በላይ ብቁ የሰው ሃይል፣ በቴክኖሎጂና በፋይናንስ አቅም ራሱን ለማጠናከር መስራት እንደሚገባው አመላክተዋል። በተቋሙ እየተዘጋጀ ያለውን አዲስ የሰራተኞች መተዳደሪያ ረቂቅ ደንብ በግብዓት ለማዳበር የሚያስችል ግንዛቤ መፈጠሩን ጠቅሰዋል።   የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው መድረኩ ኢዜአ ያለበትን ጉድለት እየፈተሸ ተልእኮውን እንዲያሳካ ገንቢ ግብዓት የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። "ኢዜአ ራሱን መመልከት ያለበት ከዓለም አቀፍ አቻ ተቋማት ጋር ነው" ያሉት አቶ ሰይፈ፤ በተለይም በሀገር ገፅታ ግንባታ ላይ የሚጠበቅበትን ሚና መወጣት የሚያስችለውን አቅም ለመፍጠርና ተወዳዳሪ ለመሆን እየሰራ ነው ብለዋል።   ተቋሙ ህጎችና አሰራሮችን ከማሻሻል ጀምሮ ዘርፈ ብዙ የለውጥ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የተናገሩት አቶ ሰይፈ፤ በተለይም ተልዕኮውን ለማሳካት የሚያስችለውን አቅም ለመፍጠር ከሀገር ውስጥና ከውጭ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በሰው ሃይል አቅም ግንባታና ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።
ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ ትብብር አጠናክራ ትቀጥላለች - አምባሳደር ጃኦ ጂዩዋን
Mar 23, 2023 115
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ጃኦ ጂዩዋን ገለጹ። በቅርቡ በኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት ልዑክ በቻይና ያደረገው ይፋዊ የስራ ጉብኝት የአገራቱን ግንኙነት በማጠናከር በኩል ትልቅ ድርሻ አለው ብለዋል። ልዑኩ በቆይታው ከቻይና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ጋር የሁለቱ አገራት ግንኙነት ሊጠናከር በሚችልባቸው በርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን ነው የተናገሩት። የንግድና ኢንቨስትመንት፣ የመሰረተ-ልማት ግንባታ ግንኙነቱን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ምክክር መደረጉን ጠቅሰው የብድር ማስተካከያ አስፈላጊነትን በተመለከተም የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል። የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በጤና፣ በኃይል ልማትና በማዕድን ዘርፍ ተሳትፏቸው የበለጠ እንዲጠናከር የማበረታታት ሥራው እንደሚቀጥል ማረጋገጫ ተሰጥቷል ብለዋል። በተጨማሪም የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ ትብብሩን ማሳለጥ የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ እንዲዋቀር ሥምምነት ላይ መደረሱንም አንስተዋል። እያደገ የመጣውን የሁለቱ አገራት የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ አምባሳደሩ አረጋግጠዋል። ዘንድሮ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ሥራዎችን ለማከናወን ቻይና የቀረጸችው "የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ" 10ኛ ዓመቱን እንደሚይዝ ገልጸው ኢትዮጵያ በእነዚህ ዓመታት ጠንካራ ግንኙነት እንደነበራት አስታውሰዋል። በቀጣይም በኢኒሼቲቩ ማዕቀፍ በኢትዮጵያ የሚካሄዱ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎችን ለማሳለጥና ትበብሩን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰራ ገልጸዋል። በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን አጋርነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመው በተለይም የኢትዮጵያ ተማሪዎች በቻይና በዘርፉ የሚሰጣቸውን የሥልጠና እድል ለማስፋት ትኩረት ተደርጓል ብለዋል። የቻይና ሥመ-ጥር የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ሥራ ተሳትፏቸውን ለማጠናከር እንደሚሰራም ገልጸዋል። በሌላ በኩል በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተከስቶ የነበረው ጦርነት በሰላም ሥምምነት መቋጨቱን ቻይና በአድናቆት እንደምትመለከተው ገልጸው ሥምምነቱ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ሰላም ለአፍሪካ ቀንድና ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም ወሳኝ ነው ያሉት አምባሳደር ጃኦ ጂዩዋን ሥምምነቱ ይህንን በማረጋገጥና ኢትዮጵያን ወደ ቀድሞ ሰላምና የአኮኖሚ ግንባታ ሥራ ለመመለስ አበርክቶው ከፍተኛ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባትና ለችግር ለተጋለጡ ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ ለማቅረብ የሚያደርገውን ጥረት በመደገፍ ቻይና ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን ትቆማለች ነው ያሉት። የመልሶ ግንባታ ሥራው ከተጠናቀቀ በኋላ የቻይና ባለሃብቶች በእነዚህ አካባቢዎች በኢንቨስትመንት ሥራ እንዲሰማሩ ለማድረግም ጥረት ይደረጋል ብለዋል። ቻይና የዓለምን ሰላም ለማረጋገጥ ባለፈው ዓመት ያወጣችውን "ዓለም አቀፍ የደኅንነት ኢኒሼቲቭ" መሰረት በማድረግ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በመተባበር በአፍሪካ ቀንድና በምስራቅ አፍሪካ ሰላምና መረጋጋት ለማጽናት በቅንጅት እንደምትሰራ ተናግረዋል። እንደ አወሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2022 በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ 2 ነጥብ 19 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን በኢትዮጵያ የቻይና ቀጥታ ኢንቨስትመንትም 3 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። የኢትዮጵያና የቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1970 ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳድር አድርገው ሾሙ
Mar 23, 2023 222
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳድር አድርገው ሾመዋል። የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 62 (9) እና በአዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀፅ 14/2/ለ/ መሠረት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት፤ እንዲሁም በኢፌዴሪ መንግሥት እና በህወሓት መካከል ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እና ግጭትን ለማቆም በፕሪቶርያ ደቡብ አፍሪካ በተደረገው የሰላም ስምምነት አንቀጽ 10(1) መሠረት አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም በማስፈለጉ፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በመጋቢት 9/2015 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ “የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር ደንብን አፅድቋል። በዚሁ ደንብ አንቀጽ 3(2) መሠረት የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳድር አድርገው ሾመዋል። ርዕሰ መስተዳደሩ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎችን ውክልና የሚያረጋገጥ እና አካታች የሆነ አስተዳደር በማዋቀር የክልሉን አስፈፃሚ አካል የመምራት እና የማስተባበር ኃላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
አስፈጻሚው አካል ሀላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ ምክር ቤቱ የተጠናከረ ቁጥጥርና ክትትል እያደረገ ነው---ቋሚ ኮሜቴዎች 
Mar 22, 2023 110
ሀዋሳ መጋቢት 13/2015 (ኢዜአ) አስፈጻሚው አካል ሀላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ ምክር ቤቱ የቁጥጥርና ክትትል ሥራ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ገለጹ። ሰብሳቢዎቹ በምክር ቤቱ የሚወጡ ህጎች፣ አዋጆችና ደንቦች በትክክል ሥራ ላይ መዋላቸውን በመገምገም ክፍተት ሲኖርም ፈጥኖ እንዲታረም የማድረግ ሥራ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ ሙስናና ብልሹ አሰራሮች እንዲታረሙ ትኩረት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በሲዳማ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ህጻናት፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ አየለች ሌዳሞ እንዳሉት፣ አስፈጻሚው አካል የተጣለበትን ሀላፊነት በአግባቡ እንዲወጣ ኮሚቴው አስፈላጊውን ክትትልና ቁጥጥር ያደርጋል። "በእዚህም ቋሚ ኮሚቴው የሚከናወኑ ጉዳዮችን በመገምገም ያሉትን ጥንካሬዎችና ጉድለቶች ለይቶ ግብረ መልስ ይሰጣል" ያሉት ሰብሳቢዋ፣ በተሰጠው ግብረ መልስ መሰረት ጉድለቶች መታረማቸውን ክትትል እንደሚደረገም አስታውቀዋል። በሴቶችና ሕጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ከመከላከል አንጻር ለሚመለከታቸው አስፈጻሚ አካላት ተገቢ ድጋፍ በማድረግ ጥቃቶችን ቀድሞ ከማስቆም አንጻር ጥሩ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ከሴቶች ተጠቃሚነት አንጻር በክልሉ ጥሩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን በተደረገው ክትትል መረጋገጡን የገለጹት ወይዘሮ አየለች፣ "በአሰራር የገጠሙ ጉድለቶች እንዲታረሙ በቋሚ ኮሚቴው በኩል በቂ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ነው" ብለዋል። ሰብሳቢዋ እንዳሉት ከአገልግሎት አሰጣጥና ሙስና ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመገምገምና አስተያየት በመስጠት የህዝቡ ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝም በትኩረት እየተሰራ ነው። በምክር ቤቱ የህግ፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዮሴፍ ዮሳ በበኩላቸው እንዳሉት የምክር ቤቱ አባላትና ቋሚ ኮሚቴው አስፈጻሚውን አካል ከመከታተል፣ ከመቆጣጠርና ከመደገፍ በተጨማሪ የወጡ ህጎች በአግባቡ ሥራ ላይ መዋላቸውን ይከታተላሉ። በክልሉ ምክር ቤት የተለያዩ አዋጆች እንደሚወጡ ያስታወሱት አቶ ዮሴፍ "ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በትክክል ሥራ ላይ ውለው ያመጡትን ለውጥ ክትትል ይደረጋል" ብለዋል። በዚህ በኩል በክልሉ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ መልካም የሚባል መሆኑን ገልጸው፣ ኮሚቴው የተሰጠውን ሃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት ያደረጋቸው የክትትል ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልቅ ስጋት እየሆነ የመጣውን ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ የምክር ቤቱ አባላት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የክልል ጥያቄን ተከትሎ በነበረው የሽግግር ጊዜ ግርግሩን ተጠቅሞ የተሰሩ የሙስና ወንጀሎች እንዳሉ የተናገሩት አቶ ዮሴፍ፣ ይህን በተገቢው መንገድ ተከታትሎ ለማረምና የተመዘበረ ሀብት ለማስመለስ ምክር ቤቱ በትኩረት መስራቱንም አመልክተዋል። በእዚህም ባለፉት ሰባት ወራት ከምዝበራ ጋር በተያያዘ በተደረገ የኦዲት ግኝት 21 ሚሊዮን ብር ተመላሽ መደረጉንም አቶ ዮሴፍ ገልጸዋል። "ከዚህ ባለፈ 100 የሚሆኑ አመራሮች፣ የስራ ሀላፊዎች እና ሠራተኞች በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል" ብለዋል። የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚጎዱ ተግባራት ተጠያቂነት ባሰፈነ መልኩ በአግባቡ እንዲታረሙ ምክር ቤቱ የሚያደርገው ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር ሁለተኛ የስራ ዘመን አራተኛ መደበኛ ጉባዔ በሃዋሳ ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሕወሓት ላይ አሳልፎ የነበረውን የሽብርተኝነት ውሳኔ አነሳ
Mar 22, 2023 172
አዲስ አበባ መጋቢት 13/2015 (ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ላይ አሳልፎ የነበረውን የሽብርተኝነት ውሳኔ አነሳ። የሕወሓት ከአሸባሪነት መነሳት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በፌደራል መንግሥትና በሕወሓት መካከል የተደረሰውን የሠላም ሥምምነት ተግባራዊነት ለማፋጠን ይረዳልም ተብሏል። በምክር ቤቱ የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ ሕወሓት ከአሸባሪነት መዝገብ እንዲነሳ ያስፈለገበትን ምክንያት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ በአገሪቷ ዘላቂ ሰላም እየሰፈነ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ይህም ለኢትዮጵያ ህዝብ እፎይታ የሰጠ ነው ብለዋል፡፡ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ህወሓት ሲከተለው ከነበረው ኢህገ-መንግስታዊ እና በሽብር እንዲፈረጅ ያደረጉትን ተግባራት እያሻሻለ መምጣቱንም ጠቁመዋል፡፡   በሰላም ስምምነቱ ወቅት መግባባት ላይ የተደረሱባቸው ነጥቦችም ፍሬ ማፍራት መጀመራቸውን የተናገሩት አቶ ተስፋዬ በልጂጌ፤ ስምምነቱን በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ምክር ቤቱ ከዚህ ቀደም በሕወሓት ላይ አሳልፎ የነበረውን የአሸባሪነት ውሳኔ እንዲያነሳ ጠይቀዋል፡፡ ይህም እንደ አገር ዘላቂ ሰላምን ለመገንባትና ልዩነቶችን በሰለጠነ መልኩ ለመፍታት አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ምክር ቤቱም ከዚህ ቀደም አሳልፎት የነበረውን የአሸባሪነት ውሳኔ በማንሳት የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲደረግ የበኩሉን እንዲወጣ የውሳኔ ሃሳብ አቅርበዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የምክር ቤቱ አባላት፤ ኢትዮጵያ ወደ ዘላቂ ሰላም እንድታመራ ከዚህ ቀደም ተላልፎ የነበረው ውሳኔ መነሳቱ ተገቢ ነው ብለዋል፡፡ ይህም የሰላም ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግና የተጀመረውን የሰላም ሂደት ለማጽናት ያግዛል ነው ያሉት፡፡ የውሳኔ ሃሳቡን በመቃወም አስተያየታቸውን የሰጡ የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው በሰላም ስምምነቱ መሰረት ሕወሓት ትጥቅ ባልፈታበት ሁኔታ ከአሸባሪነት መዝገብ ማንሳት በአገር ላይ አደጋ ሊፈጥር እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ሕወሃት ከአሸባሪነት መዝገብ ከመነሳቱ በፊት የሰላም ስምምነቱ አተገባባር ለምክር ቤቱ ቀርቦ መገምገም እንዳለበት አንስተው፤ የውሳኔ ሃሳቡን ተቃውመዋል፡፡   የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በምላሻቸውም ህወሃትን ከአሸባሪነት መዝገብ ማንሳት የሰላም ስምምነቱን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም፣ ስምምነቱን ሳይሸራረፍ ተግባራዊ ለማድረግ እና የተጀመረውን የሰላም ሂደት ለማጽናት ትልቅ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በሰላም ስምምነቱ መሰረት የሕወሓት ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታት ሂደት ከከባድ መሳሪያዎች መጀመሩን ጠቅሰው፤ ሕወሃትን ከአሸባሪነት መዝገብ ማንሳት ይህን ስራ ለማጠናከር እንደሚያግዝ አመልክተዋል። በመሆኑም የምክር ቤቱ አባላት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ እንዲያጸድቁ ጠይቀዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በውሳኔ ሃሳቡ ላይ ጥልቅ ውይይት ካደረጉ በኋላ በአብላጫ ድምጽ አጽድቀዋል፡፡፡    
ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት አገርን ለመገንባት  ለጸረ ሙስና ትግሉ ውጤታማነት ሁሉም  ኃላፊነቱን  ሊወጣ ይገባል
Mar 22, 2023 118
አዲስ አበባ መጋቢት 13/2015 (ኢዜአ) ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት አገርን ለመገንባት ለጸረ ሙስና ትግሉ ውጤታማነት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ የፌደራል ሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ በፌዴራል ተቋማት ስር ለሚገኙ ለስነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ክፍል፣ ለውስጥ ኦዲት አገልግሎት፣ለሕግ አገልግሎት እና ለተቋማት ለውጥ ስራ አመራር ኃላፊዎች ያዘጋጀው ስልጠና ዛሬ በቢሾፍቱ ተጀምራል። በስልጠናው የዩኒቨርስቲዎች ሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ክፍል ኃላፊዎችም ተሳትፈዋል። የፌደራል ሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወዶ አጦ ሙስና ኢትዮጵያ ከተጋረጡባት ዋንኛ ችግሮች መካከል አንዱ መሆኑንና እየቀያየረ ያለው ሙስና የኢኮኖሚ እድገትን በመግታት ፣አንድነትን በማናጋት ስርዓተ መንግስቱን ለመናድ አደጋ የሚጋርጥ መሆኑን ገልጸዋል ። ችግሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የደህንነት ስጋት በመሆኑ መንግስት ሙስናን ለመታገል ብሔራዊ ኮሚቴ አዋቅሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ጠንካራ ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት አገር ለመገንባት የተጀመረው የፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል። ሁሉም የፀረ-ሙስና ትግሉ ባለቤት መሆን እንዳለበትም ነው ምክትል ኮሚሽነሩ ያመለከቱት። ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ከ260 በላይ የፌደራል ተቋማት የስራ ኃላፊዎች መሳተፋቸው ተገልጿል።
ማህበራዊ
የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የመደመር ትውልድን ግንባታ እንዲደግፍ ጥሪ ቀረበ
Mar 23, 2023 89
አዲስ አበባ መጋቢት 14/20115 (ኢዜአ)፦ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ባለው ተቋማዊ አቅም የመደመር ትውልድን ግንባታ እንዲደግፍ ጥሪ ቀረበ። አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ መደመር የኢትዮጵያን እምቅ አቅም በማሰባሰብ ሀገርን ወደ ከፍታ ለማሻገር በለውጡ የተወለደ የፖለቲካ ዕይታና ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰዋል።   መደመር ግቡ ያለፉ ጠባሳዎቻችንን ማከም፣ ችግርቻችንን በአገር በቀል እውቀት በጋራ መፍታት ነው ሲሉም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲሱ የመደመር ትውልድ መፅሃፋቸው የመደመር ትውልድ ከትናንት በመማር በጋራ ጥረታቸው ጠንካራዋንና የበለፀገች ኢትዮጵያን መገንባት እንዳለባቸው መክረዋል ብለዋል።   የጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በበኩላቸው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር እሳቤና የመደመር ትውልድ መጻህፍትን ሀገርና ዓለምን ለመጥ ቀም በማሰብ ለንባብ እንዳበቁ ተናግረዋል። መደመር ያለፉ ውስብስብ ሀገራዊ ችገሮችን በጋራ መፍታትን፣ ዓለም ቀፋዊ ትብብር ማጠናከርን የሚያስገነዘብ መሆኑንም ጠቅሰዋል።   ከመጻሕፍቱ ሽያጭ የሚገኘው ገንዘብ ለትውልዱ የሚጠቅሙ ፕሮጀክቶችን በማልማት ላይ እየዋለ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የመደመር ትውልድ መፅሐፍ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመፅሐፉ ሽያጭ የቱሪዝም ስፍራዎችን እና የወጣቶች የመዝናኛ ስፍራዎችን ለመገንባት እንዲውል መወሰናቸውን ሀላፊዋ አውስተዋል።   ዓለም አቀፉ ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብም የመደመር ትውልድን በመገንባት ረገድ ሚናውን እንዲወጣ ጠይቀዋል። የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ መፅሐፉን በመግዛት በኢትዮጵያ የልማት ስራዎች ላይ አሻራውን እንዲያሳርፍ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ሀላፊዋ ጥሪ አቅርበዋል።   የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ መሆኑን የተናገሩት በመፅሐፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ ናቸው። የመደመር እሳቤ ዓለም አቀፋዊ መርሆን ያገናዘበ በመሆኑ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ እንደ የአውዱ ሊጠቀምበት እንደሚችልም ጠቁመዋል።
የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ ነው - ዶክተር ምህረት ደበበ
Mar 23, 2023 112
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) የመደመር ትውልድ አቅምን አሰባስቦ አገርንና ዓለምን የመለወጥ ልህቀትን የሚሻና ለስኬቱ የሚተጋ ነው ሲሉ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ ተናገሩ።   "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ የእንግሊዝኛ ቅጂ የሆነው "Generation Medemer"ን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የማስተዋወቂያ መርሃ-ግብር በወዳጅነት ፓርክ ቁጥር ሁለት እየተካሄደ ነው።   የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ የመደመር ተከታታይ መጻሕፍት የያዟቸውን ፍልስፍናና የለውጥ እሳቤዎች ላይ ዳሰሳ አቅርበዋል። መደመር እሳቤ መሆኑን ጠቅሰው ጠቅላይ ሚኒስተሩ በመፅሃፋቸው የህይወት ተሞክሯቸውንም እንዳቀረቡ ነው ያነሱት። መደመር እያንዳንዱን ሃብት እውቀት ጉልበት እሳቤ ጊዜ አሰባስቦ ለለውጥና ለእድገት መጠቀምን ያሳያል ብለዋል።   የመደመር ትውልድ ፍቅርና መተባበር፣ ስሜትና አስተውሎት፣ መተማመንን የሚገነባ ማህበራዊ መሠረትን መገንባት፣ ልህቀትን መሻት መገለጫዎቹ ናቸው ብለዋል። መልካም ሥነ-ምግባር የመደመር ትውልድ ዋነኛ ባህሪ መሆኑን ተናግረው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመፅሐፋቸው የመደመር ትውልድ አምስተኛውና በተዋረዳዊ ቅብብሎሽ የመጣ መሆኑን አብራርተዋል ነው ያሉት። የዚህ ዓለም ትውልድ በመደመር እሳቤ መተባበርና ያለውን ሁለገብ አቅም ለጋራ ብልፅግና መጠቀም እንዳለበት የሚያትት ነው ብለዋል።   ያለንበት ዘመን ሉላዊነት፣ ጂኦ ፖለቲካ፣ ቴክኖሎጂ ያስተሳሰረው በመሆኑ የመደመር ትውልድም ከሀገር አልፎ ዓለም አቀፋዊነትን የሚያቀነቅን ሊሆን እንደሚገባው መጥቀሳቸውን አትተዋል። መደመር በአንድነት አገርን ወደ ከፍታ የማሻገር መንገድን የሚያሳይ መነፅር መሆኑን ጠቅሰዋል። የመደመር እሳቤ ዓለም አቀፋዊ መርሆን ያገናዘበ በመሆኑ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ እንደየአውዱ ሊጠቀምበት የሚችል ነው ብለዋል።
በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ምግብና መድሃኒቶችን በመቆጣጠሩ ረገድ የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ ነው - የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን
Mar 23, 2023 63
ሐረር መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ምግብና መድሃኒቶችን በመቆጣጠሩ ረገድ የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ስድስት ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማውን በሐረር ከተማ እያካሄደ ነው። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ በግምገማው መድረክ እንደተናገሩት፤ በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ምግብና መድሃኒቶችን ለመቆጣጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።   በተለይ ገበያ ላይ ያሉ ምርቶች ትክክለኛ መስፈርት ያላሟሉ፣ የደረጃ ምልክት ያለጠፉ፣ የምርትና አገልግሎት ማብቂያ ዘመን በውል በማይታወቁ ምርቶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ የማስወገድ ስራ መከናወኑን ገልጸዋል። እንዲሁም የብቃት ደረጃ ሳይኖራቸው ምርት ባመረቱ ድርጅቶች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ከመውሰድ ባሻገር በህግ እንዲጠየቁ የማድረግ ስራ ማከናወኑን ነው ዋና ዳይሬክተሯ ያመለከቱት። በተለይ በኮንትሮባንድ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ ሲሉ ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በመሆን በርካታ ምግብና መድሃኒት እንዲሁም ሲጋራ በቁጥጥር ሰር መዋላቸውን ጠቅሰው፤ ይህም ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሯ ገለጻ ህገ-ወጥ የምግብና መድሃኒት ንግድ እንዲሁም ምግብን ከባዕድ ነገሮች ጋር ቀላቅሎ ለገበያ ማቅረብ አሁንም ፈተና እየሆነ እንደሚገኝና ይህንን ለመቆጣጠር የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። በሐረሪ ክልል የምግብና መድሃኒት ቁጥጥርና ጥራት ከማስጠበቅ አንጻር ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ያሲን አብዱላሂ ገልጸዋል። ከትንባሆ ቁጥጥር ጋር በተያያዘም ቢሮው ግብረ-ሃይል አቋቁሞ የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በክልሉ 119 የህክምና መሳሪያና የመድሃኒት ጅምላ አከፋፋይ፣ የመድሃኒት መደብርና ምግብ አምራችና አከፋፋዮች እንደሚገኙም አቶ ያሲን ጠቁመዋል። ባለስልጣኑ ለሁለት ቀናት በሚቆየው የግምገማ መድረክ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የፌዴራልና የክልሉ ምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ተቋማት ሃላፊዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ሐሰተኛ ሰነድ አቅርበሻል በማለት ከአንዲት ግብር ከፋይ 70ሺህ ብር ጉቦ የተቀበለ የገቢዎች ባለሙያ እጅ ከፍንጅ ተያዘ
Mar 23, 2023 74
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፦ ሐሰተኛ ሰነድ አቅርበሻል በማለት ከአንዲት ግብር ከፋይ ግለሰብ 70ሺህ ብር ጉቦ የተቀበለ የገቢዎች ባለሙያ እጅ ከፍንጅ ተያዘ። በወንጀሉ ተባባሪ የሆነ አንድ ባለሙያ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የአነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት የአወሳሰን ባለሙያ የአንድ ሠራተኛ የቅርጫፍ ጽህፈት ቤቱ ግብር ከፋይ የሆኑ ግለሰብን ካቀረብሽው 10 ደረሰኞች መካከል 8ቱ የተበላሹ በመሆኑ ወደ አጣሪ ኮሚቴ መላኩን እና ሁለቱ ደግሞ እጄ ላይ ይገኛሉ በማለት ጉዳዩን ለማዳፈን ግን 100ሺህ ብር ጉቦ እንዲሰጠው መጠየቁን ፖሊስ ገልጿል። የግል ተበዳይ ያቀረቧቸው ሰነዶች ትክክለኛ እንደሆኑ ለማስረዳት ቢሞክሩም ባለሙያው ሳይቀበላቸው መቅረቱንም አክሎ አስታውቋል። የአወሳሰን ባለሙያ የሆነው ግለሰቡ በቢሮ ስልክ ደጋግሞ በመደወል የግል ተበዳይን በማስጨነቅ በሕግ እንደሚጠየቁ በማስፈራራት 70ሺህ ብር ለመቀበል መስማማቱንም ፖሊስ ጠቁሟል። የግል ተበዳይ ጉዳዩን ለተቋሙ ኃላፊዎች በማሳወቅ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የደንበል አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ባደረገው ክትትል በቅርጫፍ ጽህፈት ቤቱ የአወሳሳን ባለሙያ የሆነው ሙያተኛ 22 አካባቢ ከሚገኘው መስቲ ሬስቶራንት አካባቢ መጋቢት 13 ቀን 2015 ዓ.ም ገንዘቡን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ መያዙንም አስታውቋል። የወንጀሉ ተባባሪ የሆነው በተቋሙ የጥቆማ አቀባበል ባለሙያ ከፍተኛ ኦፊሰር የሆነው ሠራተኛ በተመሳሳይ ቀን በጉቦ የተገኘውን ገንዘብ ሲቀበል መገናኛ አካባቢ እንደተያዘ የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ አመልክቷል። ማኅበረሰቡ መሰል ወንጀል ፈፃሚዎችን ለሕግ አካላት አጋልጦ የመስጠት ልምዱ ይበል የሚያሰኝ መሆኑንም ገልጿል። ወደፊትም የሕዝብን እና የመንግሥትን እምነት በማጉደል በማኅበረሰቡ ላይ በደል የሚፈጽሙ አካላትን ወደ ሕግ ለማቅረብ የሚደረገው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብሏል ፖሊስ በመረጃው።
ኢኮኖሚ
በግብርና ዘርፍ ሴቶችን ያማከለ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ እንደሆነ የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ
Mar 23, 2023 79
ባህር ዳር መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ በግብርና ዘርፍ ሴቶችን ያማከለ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ የኢኮኖሚ አቅማቸውን የሚያጠናክሩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በአማራ ክልል ሰሜን ሜጫ ወረዳ የሴቶችን የግብርና ተሳትፎ የሚያሳይ ጉብኝት ተካሄዷል። በጉብኝቱ የተሳተፉት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሶፊያ ካሳ እንዳሉት፤ ሴቶች በግብርናው መስክ በተገቢው መንገድ ከታገዙና ከተደገፉ ከኢኮኖሚ ጥገኝነት የሚላቀቁበት እድል ሰፊ ነው። ለዚህም ሴቶችን በግብርና ኤክስቴንሽን ተጠቃሚ በማድረግ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።   በተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ የግብዓት አቅርቦት፣ የሙያ እገዛ፣ የገበያ ትስስር መፍጠርና ሌሎች ድጋፎችን ሴቶች እንዲያገኙ አሰራር ተቀምጦ እየተተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ሴቶች ከተደገፉ የተሻለ ለውጥ እንደሚያስመዘግቡ በሰሜን ሜጫ ወረዳ በግብርና መስክ የተሰማሩ ሴቶች ያስመዘገቡት ውጤት ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፤ ድጋፉን ማሳደግ ላይ ቀሪ የቤት ስራዎች በትኩረት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። ይህን ለማጠናከር በአማራና ሲዳማ ክልል የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ተቀርፆ መተግበር መጀመሩን ጠቅሰው፤ ፕሮጀክቱ ሴቶችን በተለየ ሁኔታ የማብቃትና የማገዝ ስራ እያከናወነ እንደሆነ ጠቁመዋል።   የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የስርዓተ ፆታ ባለሙያ ወይዘሮ ማስተዋል ካሳሁን በበኩላቸው በክልሉ ሴቶች በግብርናው ዘርፍ ንቁ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው ብለዋል። በክልል ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን የሚበልጡ ሴቶችን በማካተት የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም በቀበሌ ደረጃ ጭምር ለሴቶች በቅርበት እገዛና ድጋፍ የሚያደርግ ባለሙያ ተመድቦ ሙያዊ እገዛ በመስጠት የግብርና ግብዓትና የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የሃብት አጠቃቀምና የስራ ክፍፍል እንዳይኖር ግንዛቤ እንዲያገኙ እየተደረገ ሲሆን በተሰራው ስራም ለውጥ እየመጣ መሆኑን አመልክተዋል።   በሰሜን ሜጫ ወረዳ በ9 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እየተከናወነ ባለው የበጋ ወራት የመስኖ ልማት እንቅስቃሴ 2 ሺህ 500 ሴቶች እየተሳተፉ ነው ያሉት ደግሞ የወረዳው ግብርና ፅህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ እስጢፋኖስ ስሜነህ ናቸው። ሴቶች የማዳበሪያና ምርጥ ዘር ግብዓት እጥረት እንዳይገጥማቸው በቀበሌ ባለሙያ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በሰሜን ሜጫ ወረዳ እናምርት ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ሴት አርሶ አደር መልሽው ሞላ እንዳሉት፤ በግብርና ባለሙያዎች በሚደረግላቸው ድጋፍ ቃሪያ፣ ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ አቮካዶና ስንዴ እያለሙ ነው። አሁን ካለሙት ጥቅል ጎመን ብቻ በመጀመሪያ ሽያጭ 13 ሺህ ብር ማግኘታቸውን ጠቅሰው፤ በጠቅላላ ካለሙትም ከ100 ሺህ ብር በላይ ገቢ እንደሚጠብቁ አስታውቀዋል። በጉብኝቱ ከፌደራል ግብርና ሚኒስቴርና ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተውጣጡ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የአማራ ክልል ህብረት ስራ ማስፋፊያ ባለስልጣን በክልሉ የሰብል ምርት ዋጋን ለማረጋጋት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Mar 23, 2023 60
ባህር ዳር መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል እየናረ የመጣውን የሰብል ዋጋ ለማረጋጋት የሰብል ምርት በትስስር ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ህብረት ስራ ማስፋፊያ ባለስልጣን አስታወቀ። መርከብ ዩኒየን በባህር ዳር ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች 1ሺህ 700 ኩንታል የሰብል ምርት በቅናሽ ዋጋ ማሰራጨት ጀምሯል።   በዚህ ወቅት የባለስልጣኑ ሃላፊ አቶ ጌትነት አማረ እንደገለጹት፤ ህብረት ስራ ማህበራት 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በጀት መድበው የሰብል ምርት በመግዛት የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት እየሰሩ ይገኛሉ። እስካሁን ከ731ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ግዥ መፈፀሙን ጠቅሰው፤ ከዚህ ውስጥ 174ሺህ ኩንታል የሰብል ምርት በትስስር ለገበያ መረጋጋት እንዲውል መደረጉን ገልጸዋል። እየናረ የመጣውን የሰብል ምርት ዋጋ ለማረጋጋት ትርፍ አምራች በሆኑ አካባቢዎች የሚገኙ ዩኒየኖችና ህብረት ስራ ማህበራት በተመጣጣኝ ዋጋ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ የጋራ መግባባት ተፈጥሮ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ኢብራሂም መሀመድ በበኩላቸው፤ የህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች ገበያው እንዲረጋጋ የሰብል ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ህብረተሰብ እንዲያቀርቡ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ በባህር ዳር ከተማ የሚገኘው የመርከብ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበር ዩኒየን ባሳየው ቁርጠኝነት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጤፍ፣ በቆሎና የዳቦ ዱቄት ማቅረብ መጀመሩ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል። ሌሎች ዩኒየኖችና የህብረት ስራ ማህበራትም ይህንን አርአያነት ወስደው በየአካባቢያቸው ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ የሰብል ምርት በማቅረብ ዋጋውን ማረጋጋት እንዳለባቸው አመልክተዋል። ፋብሪካዎችም በቂ የስንዴ ምርት እንዲያገኙ ይሰራል ያሉት ዶክተር ኢብራሂም፤ የሸማች ህብረት ስራ ማህበራትም ምርቱን ለህብረተሰቡ በፍትሃዊነት ተደራሽ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። በቀጣይ አንድ ወር ውስጥ 10ሺህ ኩንታል የጤፍ፣ የበቆሎና የዳቦ ዱቄት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን የመርከብ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው እሸቱ አስታውቀዋል። ለባህር ዳር ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ የሚሆን አንድ ሺህ 700 ኩንታል ምርት በገበያ ከሚሸጠው ከ600 እስከ 1ሺህ ብር ቅናሽ ማከፋፈል ተጀምሯል ብለዋል። የልደታ ሸማቾች ህብረት ስራ ማህበር ሰብሳቢ ወይዘሮ ውብርስት እንዳለው፤ ከዩኒየኑ የተረከቡትን 40 ኩንታል የጤፍና የዳቦ ዱቄት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚያሰራጩ ተናግረዋል። በቀጣይም ማህበሩ በትስስር የሚያገኘውን ምርት በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ነዋሪዎች በፍትሃዊነት በማሰራጨት ገበያው እንዲረጋጋ የድርሻቸውን እንደሚወጣ ገልጸዋል።    
በኢትዮጵያ የሸማቾችን መብት የሚያስጠብቁ የሸማቾች ማኅበራትን የመደገፍ ሥራ እየተሰራ ነው - የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
Mar 23, 2023 60
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) በኢትዮጵያ የሸማቾችን መብት የሚያስጠብቁ የሸማቾች ማኅበራትን የመደገፍ ሥራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ። ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዓለም አቀፉን የሸማቾች መብት ቀን በፓናል ውይይት አክብሯል። ቀኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ40ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ10ኛ ጊዜ "በደረሰኝ ግብይት ይፈጽሙ፤ መብትዎን ያስከብሩ" በሚል መሪ ኃሳብ ተከብሯል። ቀኑ ሸማቹ ያለው መብት ምን ድረስ ነው?፣ ችግር ሲገጥመው መብቱን እንዴት ማስከበር ይችላል? በሚሉ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማን ያነገበ ነው። በውይይቱ ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን የሸማቾች መብት፣ የነጋዴው ማኀብረሰብ ግዴታ እንዲሁም ችግሮች ላይ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ደኤታ አቶ እንዳለው መኮንን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የሸማቹ መብት ሊከበር የሚችለው ሸማቹ በቅድሚያ ሕጋዊ መንገድን ተከትሎ ግብይት ሲፈጽም ነው። "ግብይት በምፈጽምበት ጊዜ መብቴ ተጥሷል የሚል ሸማች ግዥ የፈጸመበትን ደረሰኝ በማቅረብ እርምጃ እንዲወሰድ ማድረግ ይገባዋል" ያሉት ሚኒስትር ደኤታው አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ግን ይህ ሲሆን አይታይም ብለዋል። በቅርቡ ከሲሚንቶ ምርት ጋር በተያያዘ ከፋብሪካ የሚወጣበት ዋጋ በመንግሥት የተተመነ ቢሆንም በአግባቡ ተግባራዊ እየሆነ አይደለም፤ ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ሸማቹ ሕግን ባለማክበሩ መሆኑን አመልክተዋል። ያለደረሰኝ ግብይት መፈጸም ሕገ ወጦችን ለመያዝ የሚደረገውን እንቅስቃሴ አዳጋች ከማድረጉም ባለፈ የምርቶችን ደኅንነትና ጥራት ለማረጋገጥ የማያስችል መሆኑን አብራርተዋል። ጉዳዩ ለመንግሥት ወይም ለተወሰኑ አካላት ብቻ የሚተው ሳይሆን ሁሉም ዜጋ የመፍትሄ አካል መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ማኅበረሰብ አንቂዎች ሸማቾችን ማንቃት ላይ ትኩረት እንዲሰጡም ጥሪ አቅርበዋል። ሸማቹ ማኅበረሰብ በሕገ ወጥ ነጋዴዎች የሸማቾች መብት የሚጋፉ ወንጀሎች ሲፈጸሙ ለሚመለከተው አካል ጥቆማ መስጠት እንደሚገባውም ነው ሚኒስትር ደኤታው ያስገነዘቡት።   በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሸማቾች መብት ጥበቃና ግንዛቤ ዴስክ ሃላፊ ሰይፉ አየለ በበኩላቸው ወንጀሎች የሚሰሩት የት ነው?፣ በሕገ ወጥ መንገድ ክምችት የሚካሄደው የት ነው?፣ የዕቃዎች መከዘኛዎች የት ናቸው? የሚለውን ጥያቄ ሊመልስ የሚችለው ማኅበረሰቡ መሆኑን አንስተዋል። "ማኅበረሰቡ ሕገ ወጥ ነጋዴዎች በሚያጋጥሙት ጊዜ ለፍትህ አካላት የማሳወቅ ልምድ አናሳ ነው" ያሉት ሃላፊው መሰል ችግሮች ካልተፈቱ ዘላቂ መፍትሄ ማበጀት እንደማይቻል ተናግረዋል። የኛ አገር ሸማች የሚንቀሳቀሰው በተናጠል ነው ሲሉ የገለጹት ሃላፊው ለመብቱ የሚታገል ጠንካራ ሸማች ማኅበር አለመኖር ትልቅ ፈተና መሆኑን ጠቅሰዋል። በመሆኑም የሸማቾችን መብት የሚያስጠብቁ የሸማች ማኅበራትን ለማጠናከር የመደገፍ ሥራ በትኩረት እየተሰራበት መሆኑም ተናግረዋል።
የወተት ምርትን ለማሳደግ የዝርያ ማሻሻል፣ የመኖ አቅርቦትና የእንስሳት ማረፊያ ምቹነት ተቀናጅተው መተግበር አለባቸው - የዘርፉ ምሁራን
Mar 23, 2023 77
ሀዋሳ መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ የወተት ምርትን ለማሳደግ የዝርያ ማሻሻል፣ የመኖ አቅርቦትና የእንስሳት ማረፊያ ምቹነት ተቀናጅተው መተግበር እንዳለባቸው የዘርፉ ምሁራን አመለከቱ። የእንስሳት ምርታማነትን ለማሳደግ የተያዙ ዕቅዶች ስኬታማ እንዲሆኑ መንግስት፣ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ የምርምር ማዕከላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመስኩ ምሁራን አስገንዝበዋል።   በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ኮሌጅ በእንስሳት ሀብት ዙሪያ ምርምር እየሰሩ ያሉ ምሁራን ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ኢትዮጵያ ያላትን ከፍተኛ አቅም በመጠቀም ተጠቃሚ እንድትሆን በስፋት መሰራት አለበት። በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ስነ-ምግብ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አጀቡ ኑርፈታ የእንስሳት መኖ ሲዘጋጅ ምርት ለመስጠት የሚያስችሉ ንጥረ ነገሮችን መያዝ እንዳለበት አስገንዝበዋል። በመሆኑም የእንስሳቱ አመጋገብ ከእንስሳቱ የሚጠበቅን ምርት ሊሰጥ በሚያስችል መልኩ መሆን እንደሚገባው ገልጸው፤ የእንስሳት ዝርያ መረጣና የመኖ አቅርቦት ለውጤታማነት ቁልፍ ጉዳዮች እንደሆኑ ገልጸዋል። የመኖ ዝግጅት ከመጀመሪያ ጀምሮ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የገለጹት ፕሮፌሰር አጀቡ፤ የአርሶ አደሩን ህይወት ለመቀየርና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲም የእንስሳት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻዎች ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   በእንስሳትና ተፈጥሮ ግጦሽ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ በእንስሳት እርባታና ጄኔቲክስ ዘርፍ ፕሮፌሰር አበራ መለሰ በበኩላቸው እንዳሉት በዶሮ ስጋና እንቁላል ምርታማነት ላይ በዋናነት የተለያዩ ምርምሮችን ሲያደርጉ ቆይተዋል። የዶሮና እንቁላል ምርታማነትን በማሳደግ እያንዳንዱ ቤተሰብ በአነስተኛ የዶሮ እርባታ ተሳትፎ እንዲኖረው በምርምር የማገዝ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   የእንስሳት መኖ ላይ የተደረጉ የምርምር ስራዎች ውጤት እንደታየባቸው አመልክተው፤ ከዶሮ መኖ ጋር በተያያዘ በሞሪንጋ /ሽፈራው/ ተክል ላይ ያደረጉት ምርምር በመኖነት ለዶሮዎች ቢቀርብ የእንቁላል ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚያስችል መረጋገጡን ጠቁመዋል።   በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ትምህርት ክፍል ዳይሬክተር በእንስሳትና ግጦሽ ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህር፣ ተማራማሪና በወተት ዘርፍ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ስንታየሁ ይግረም በበኩላቸው በቀን እስከ 30 ሊትር ወተት የመስጠት አቅም ያላቸው ላሞች በአያያዝ ችግር ከስድስት ሊትር በላይ እንዳይሰጡ ማድረጉን ጠቁመዋል። ይህን ችግር መፍታት የሚቻለው በተገቢው መንገድ እንስሳቱን መያዝና የተመጣጠነ መኖ በማቅረብ ሲሰራ ነው በማለት ገልጸው፤ ከዝርያ በተጨማሪ የመኖና የእንስሳት ማረፊያ ትኩረት እንደሚያስፈልጋቸው ገልጸዋል።   የእንስሳትን ምርታማነት የማሳደግ ስራ የዝርያ ማሻሻል፣ የመኖ አቅርቦትና የእንስሳት ማረፊያ ምቹነት ተቀናጅተው መተግበር እንዳለባቸው ያስገነዘቡት ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ስንታየሁ፤ በተናጠል የሚካሄደው ስራ ውጤት እንደማያመጣ ገልጸዋል።   በመሆኑም ዝርያ ማሻሻል፣ በቂ መኖና ውሀ ማቅረብ፣ ለእንስሳት ማረፊያ ምቹ ስፍራ ማዘጋጀት ለምርታማነት ማደግ ቁልፍ ጉዳዮች በመሆናቸው ተቀናጅተው መተግበር እንዳለባቸው አስረድተዋል። እነዚህን ተግባራት በተገቢው መንገድ በመከተል የተሟላ ውጤት ማምጣት የሚያስችል ሙሉ ፓኬጅ መጠቀም እንደሚገባ ገልጸዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮ-ቴሌኮም በአዲስ መልክ ያበለጸገውን ቴሌ ብር "ሱፐር አፕ"ይፋ አደረገ 
Mar 23, 2023 66
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) ፦ኢትዮ-ቴሌኮም በአዲስ መልክ ያበለጸገውን ቴሌ ብር "ሱፐር አፕ" የሞባይል መተግበሪያ ዛሬ ይፋ አደረገ። ተቋሙ የቴሌ-ብር አገልግሎት ባቀረበ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለትራንስፎርሜሽንና የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑ ተገልጿል። የማህበረሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በማቅለል ረገድም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱም እንዲሁ። በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረገው መተግበሪያም ከዚህ ቀደም ከነበረው መተግበሪያ ተጨማሪ አገልግሎቶች ተካተውበት በአዲስ መልኩ መበልጸጉ ተገልጿል። መተግበሪያው ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹና አስተማማኝ መሆኑም ተጠቅሷል። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ኩባንያው አገልግሎቱን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ መምጣቱን ተናግረዋል። ኩባንያው ዲጂታል ኢኮኖሚን እውን የማድረግ ሥራን አጠናክሮ በመቀጠል ኢትዮ-ቴሌኮም በዘርፉ የመሪነት ሚናውን እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። ኃብትን በአግባቡ ለመጠቀም በቴክኖሎጂ መታገዝ ወሳኝ መሆኑን ተናግረው ፤በዛሬው እለት ይፋ የሆነውም መተግበሪያ ይህንን ያሳልጣል ነው ያሉት። መተግበሪያው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ጥቅም ላይ የሚውሉ መተግበሪያዎች በአንድ የተካተቱበት መሆኑን ገልጸዋል። ጊዜንና ወጭን በመቆጠብ ረገድ መተግበሪያው ትልቅ ሚና እንዳለውም ጠቁመዋል። አገልግሎቱን ከፕሌይ ስቶር፣ ከአፕ ስቶርና ከአፕ ጋለሪ በማውረድ መጠቀም እንደሚቻል ተመላክቷል።
ዓለም አቀፉ የቴሌኮምዩኒኬሽን ሕብረት ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚፈልግ ገለጸ
Mar 23, 2023 65
አዲስ አበባ መጋቢት 14 /2015 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉ የቴሌኮምዩኒኬሽን ሕብረት (አይሲዩ) ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር(ኢመደአ) ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚፈልግ አስታወቀ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ ከሕብረቱ የአፍሪካ ቀጣናዊ ዳይሬክተር አን ራቼል ኢን ጋር ተወያይተዋል።   ውይይቱ ሁለቱ ተቋማት በጋራ በሚሰሩባቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑ ኢመደአ በማህበራዊ ትስስር ገጽ ያሰፈረው መረጃ ያመለክታል። አቶ ሰለሞን ሶካ ተቋሙ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ ያለማቸውን ምርትና አገልግሎቶች እንዲሁም በኢትዮ ሳይበር ታለንት ልማት ማዕከል የሚገኙ ታዳጊዎች በሳይበር ደህንነት ዘርፎች ያከናወኗቸው ስራዎች አስመልክቶ ለዳይሬክተሯ ገለጻ አድርገዋል።   የዓለም አቀፉ የቴሌኮምዩኒኬሽን ሕብረት የአፍሪካ ቀጣናዊ ዳይሬክተር አን ራቼል ኢን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የኢትዮጵያን የሳይበር ደህንነት በማረጋገጥ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ለመደገፍ እያከናወነ ባለው ተግባር መደሰታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይ ሁለቱ ተቋማት ተቀናጅተው ውጤታማ ስራዎችን እንዲያከናውኑ የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል።   ሁለቱ ተቋማት የሳይበር ደህንነትን በቅንጅት በማስጠበቅ ረገድ ከአፍሪካ የሳይበር መከላከልና ምላሽ መስጫ (Africa CERT) ጋር እንዲሁም ኢመደአ በተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ጉባኤዎችንና አውደ ርዕዮች ላይ ላይ ያለውን ተሳትፎ ለማሳደግ በጋራ እንደሚሰሩ ተጠቁሟል።
የመዲናዋን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማቀላጠፍ አሰራሮችን በቴክኖሎጂ የማስደገፍ ተግባሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Mar 23, 2023 52
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) የአዲስ አበባ የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ኃብት ልማት ቢሮ ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አሰራሮችን በቴክኖሎጂ የማስደገፍ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ። ቢሮው በዘጠኝ ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ኃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ሂክማ ከይረዲን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ተቋማት ከሌብነትና ብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ለነዋሪዎች አገልግሎት መስጠት ይጠበቅባቸዋል። በከተማ አስተዳደሩ ባሉ ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻልና ቀልጣፋ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ ተደግፈው እንዲከናወኑ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በአገልግሎት አሰጣጣቸው ዛሬ የተገመገሙት ዘጠኙ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ አስደግፈው ለመስጠት እየሰሩ መሆናቸውን አንስተዋል። ለአብነትም የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት መረጃ አገልግሎት ኤጂንሲ፣ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን፣ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲና የእሳት አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለኅብረተሰቡ ወጪ ቆጣቢ፣ ቀልጣፋና ከብልሹ አሰራር የጸዳ አገልግሎት ተዳራሽ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራሮችን ለመዘርጋት ለሰራተኞቻቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል። በውሃና ፍሳሽ አግልግሎትና በሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት መረጃ አገልግሎት ኤጂንሲ በኩል የሚስተዋሉ የአገልግሎት መቆራረጦች መስተካከል እንዳለባቸው የመድረኩ ተሳታፊዎች አንስተዋል።  
ደረጃቸውን የጠበቁ የኤሌክትሮኒክስ ግብዓቶች ለአገር ውስጥ ገበያ እንዲቀርቡ እየተሰራ ነው--የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት
Mar 21, 2023 148
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015 (ኢዜአ)፦ በዓለም አቀፉ ኤሌክትሮ-ቴክኒካል ኮሚሽን ውስጥ በአባልነት በመሳተፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የኤሌክትሮኒክስ ግብዓቶች ለአገር ውስጥ ገበያ እንዲቀርቡ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት አስታወቀ።   በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ስር ለሚገኘው የኢትዮጵያ የኤሌክትሮ-ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት የኤሌክትሮኒክስና ተዛማጅ ቴክኖሎጂዎች ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ዓለም አቀፍ የኤሌክትሮ-ቴክኒካል ኮሚሽን ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ170 በላይ አባል አገራት ያሉት ሲሆን፤ ለኤሌክትሮኒክ፣ ኤሌክትሪካልና ተዛማጅ ቴክኖሎጂዎች ዓለም አቀፍ ደረጃ የሚሰጥ ተቋም ነው፡፡ በኢትዮጵያም ቴክኖሎጂዎቹ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ብሔራዊ ኤሌክትሮ-ቴክኒካል ኮሚቴ መቋቋሙ ይታወቃል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የኤሌክትሮ-ቴክኒካል ኮሚቴ ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ 205 አባላት ያሉት ሲሆን፤ 34ቱ በኤሌክትሮኒክና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሠረት በቀለ እንዳሉት፤ በሀገር ውስጥ የሚመረቱና ከውጭ የሚገቡ የኤሌክትሮኒክ እና ተዛማች እቃዎች ጥራታቸውን የጠበቁ መሆን አለባቸው፡፡   በዚህም ኢትዮጵያ የኮሚሽኑ አባል በመሆን ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉ ደረጃ በማውጣት እየሰራች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ይህም በሀገር ውስጥ የሚመረቱት ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ ሚናው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያ የሚመረቱ ኤሌክትሮኒክ ገመዶች፣ ትራንስፎርመሮች እና ሌሎች ኤሌክትሮሜካኒካል ዕቃዎች በጥራት ተመርተው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ እየዋሉ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡   ኢንስቲትዩቱ በዋናት የምርቶችን የጥራት ደረጃ የሚያወጣ ተቋም ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ደግሞ ምርቶች በተቀመጠው ደረጃ መሰረት መቅረባቸውን ያረጋግጣል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዓለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊ፣ አገራዊና ሌሎች ደረጃዎች ላይ የተቀመጡ የጥራት መስፈርቶችን ያሟሉ ከ8ሺህ 800 በላይ ምርትና አገልግሎቶች የጥራት ማረጋገጫ መስጠቱ ተገልጿል። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በዓለም አቀፍ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን የ250ሺህ ዶላር ድጋፍ ያስገነባውን የፀሐይ ኃይል ምርቶች መፈተሻ ቤተ-ሙከራ ሥራ አስጀምሯል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ አጭር፣ መካከለኛ፣ 3ሺህ ሜትር መሰናክል፣ እርምጃና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጀመረ 
Mar 22, 2023 101
አዲስ አበባ መጋቢት 13/2015 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ የአጭር፣ መካከለኛ፣ 3ሺህ ሜትር መሰናክል፣ እርምጃና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ተጀምሯል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክተር አቶ አስፋው ዳኜ ለአትሌቶች የውድድር እድል መፍጠር እንዲሁም የክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ ክለቦችና ተቋማት አትሌቶች አቋማቸውን እንዲለኩ ማድረግ የሻምፒዮናው አላማ ነው ብለዋል። በውድድሩ ላይ ከ19 ክለቦች እና ተቋማት የተወጣጡ ከ600 በላይ አትሌቶች ተሳታፊ መሆኑን ገልጸዋል።   በሻምፒዮናው መክፈቻ ላይ በሴቶች 3ሺህ ሜትር መሰናክል፣ በሴቶች ርዝመት ዝላይ እና በወንዶች ዲስከስ ውርወራ የፍጻሜ ውድድሮች ተካሄደዋል። ከፍጻሜ ውድድሮቹ በተጨማሪ ሌሎች የማጣሪያ ውድድሮች ይካሄዳሉ። ሻምፒዮናው እስከ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ይቆያል። የኢትዮጵያ አጭር፣ መካከለኛ፣ 3ሺህ ሜትር መሰናክል፣ እርምጃና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሁለት አስርት ዓመታትን እድሜ በላይ ማስቆጠሩን መረጃዎች ያመለክታሉ።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ አቻው ጋር ላለበት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ሞሮኮ አቀና
Mar 21, 2023 147
አዲስ አበባ መጋቢት 12 2015(ኢዜአ):- የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ አቻው ጋር ላለበት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ሞሮኮ አምርቷል። 23 ተጫዋቾችን ያቀፈው ብሔራዊ ቡድኑ ትናንት ማምሻውን ወደ ካዛብላንካ ማቅናቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን በኮትዲቯር አስተናጋጅነት በሚካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ከጊኒ ብሔራዊ ቡድን ጋር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታውን መጋቢት 15 እና 18 ቀን 2015ዓ.ም በሞሮኮ ያደርጋል።   የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ ከመጋቢት 6/2015 ዓ.ም ጀምሮ ልምምዳቸውን ሲያደርጉ ቆይተዋል። ዋልያዎቹ ከትናንት በስቲያ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከሩዋንዳ አቻቸው ጋር ባደረጉት የአቋም መለኪያ ጨዋታ በከነዓን ማርክነህ ግብ 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል። ለደቡብ አፍሪካው ክለብ ማሜሎዲ ሳንዳውንስ የሚጫወተው አቡበከር ናስር ከጉዳቱ ሙሉ ለመሉ ባለማገገሙ ከብሔራዊ ቡድን ስብስብ ውጪ በመሆኑ በምትኩ ለኢትዮጵያ መድን የሚጫወተው ኪቲካ ጀማ መተካቱ የሚታወስ ነው።   በተመሳሳይ ለማጣሪያው ጨዋታ ጥሪ ተደርጎለት የነበረው የሲዳማ ቡናው አጥቂ ይገዙ ቦጋለ በልምምድ ላይ ባጋጠመው ጉዳት ከብሔራዊ ቡድኑ ስብስብ ውጭ መሆኑ ይታወቃል። በይገዙ ቦጋለ ቦታ ለቅዱስ ጊዮርጊስ የሚጫወተው ቸርነት ጉግሳ ጥሪ ተደርጎለት ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅሏል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አራት ከግብጽ፣ ከማላዊ እና ከጊኒ ጋር የተደለደለ ሲሆን እስካሁን ባደረጋቸው ሁለት ጨዋታዎች በሶስት ነጥብ እና በአንድ የግብ ክፍያ ምድቡን እየመራ ይገኛል።
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ ሀገራት በተደረጉ የአትሌቲክስ ውድድሮች አሸነፉ
Mar 20, 2023 210
አዲስ አበባ መጋቢት 11/2015(ኢዜአ):- ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሳምንቱ መጨረሻ በተለያዩ ሀገራት በተደረጉ የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ድል ቀንቷቸዋል። በአሜሪካ ሎሳንጀለስ በተካሄደው የወንዶች ማራቶን አትሌት ጀማል ይመር በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት የማነ ጸጋዬ ደግሞ ሁለተኛ ሆኖ ጨርሷል።   በታይዋን ርዕሰ ከተማ ታይፔ በተደረገው የሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያኑ በቀለች ጉደታ፣ መሰረት ድንቄ እና ገበያነሽ አየለ ከአንድኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል። በቻይና ሸንዤን በተደረገ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች በቀዳሚነት አጠናቅቀዋል።   በዚህም በወንዶች አትሌት ባንታየሁ አዳነ በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ በሴቶች አገሬ ታምር በአንደኝነት ጨርሳለች። በባርሴሎና በተደረገ የማራቶን ውድድርም ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዘይነባ ይመር ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቃለች። በአሜሪካ የኒዮርክ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ደግሞ በሴቶች አትሌት ሰንበሬ ተፈሪ ሁለተኛ ሆና ውድድሯን አጠናቃለች።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን በአቋም መለኪያ ጨዋታ የሩዋንዳ አቻውን 1 ለ 0 አሸነፈ
Mar 19, 2023 164
አዲስ አበባ መጋቢት 10/2015 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከሩዋንዳ አቻው ጋር ያደረገው የአቋም መለኪያ ጨዋታን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተከናወነው ጨዋታ የአማካይ ተጫዋቹ ከነዓን ማርክነህ በ83ኛው ደቂቃ ላይ ለዋልያዎቹ የማሸነፊያዋን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል።   የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ እና ሌሎች የፌዴሬሽኑ አመራሮች እንዲሁም የእግር ኳስ ቤተሰቦች ጨዋታውን ተከታትለውታል። ጨዋታው የተዘጋጀው ዋልያዎቹ ከጊኒ ጋር ላለባቸው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ አቋማቸውን እንዲፈትሹ መሆኑን ፌዴሬሽኑ ገልጿል። በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት እ.አ.አ በ2023 በሚካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ ከጊኒ ጋር በሞሮኮ ራባት መጋቢት 15 እና 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጨዋታዋን ታደርጋለች።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ ጋር ላለበት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ከነገ በስቲያ ወደ ሞሮኮ ያቀናል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አራት ከግብጽ ፣ ማላዊ እና ጊኒ ጋር የተደለደለች ሲሆን እስካሁን ሁለት ጨዋታ አድርጋ 3 ነጥብ በማግኘት በአንድ የግብ ክፍያ ምድቡን እየመራች ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎችን ጥራትና ተደራሽነት ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል - የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
Mar 23, 2023 52
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የትንበያና የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን ጥራትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የዓለም የሚቲዎሮሎጂ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ62ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደረጃም ለ42ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተከብሯል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ክንፈ ሃይለማርያም በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎችን ለማኅበረሰቡ ተዳራሽ በማድረግ ደኅንነት ለማስጠበቅና ልማትን ለማፋጠን እየተሰራ ነው። ትክክለኛ የአየር ትንበያ መረጃዎች ለጥናት ምርምር ጭምር እንደሚያግዙ ጠቁመው ትክክለኛ የአየር ትንበያ መረጃ እንዲኖር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ጎርፍና ድርቅ ያሉ ክስተቶች በአገሪቷ እየተበራከቱ መሆናቸውን አንስተው እነዚህን ለመቋቋምም የተጠናከረ የአየር ሁኔታ መከታተያ፣ መተንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት በመገንባትና በመዘመን ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለዚህም በሰው ሃብትና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ራሱን በማሻሻል ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። በዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ ቢሮ ዳይሬክተር ዶክተር አግነስ ኪጃዚ በበኩላቸው የሚቲዎሮሎጂ ትንበያ መረጃ በተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመታገዝ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች የግብርና ሥራዎች ወቅታቸውን ጠብቀው እንዲከናወኑ ከማድረጉም ባለፈ ምርቶች በጊዜ ተሰብስበው ለተፈለገላቸው ዓላማ እንዲውሉ ከማገዝ አንጻር ሰፊ ጠቀሜታ አላቸው።    
በደቡብ ክልል የጎርፍ አደጋን ለመከላከል የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ተገለጸ
Mar 23, 2023 89
ሀዋሳ መጋቢት 14/2015 (ኢዜአ) በደቡብ ክልል እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ ተከትሎ ጎርፍና ናዳ ይከሰትባቸዋል ተብሎ በተለዩ የስጋት አካባቢዎች የቅድመ መከላከል ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጋንታ ጋምኣ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በክልሉ በዝናብ ወቅት የጎርፍና የመሬት ናዳ በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ያስከትላል። በተለይ የወቅቱን የበልግ ዝናብ ተከትሎ በክልሉ ሊከሰት የሚችለውን የጎርፍ አደጋ አስቀድሞ ለመከላከል የስጋት አካባቢዎችን እስከ ቀበሌ ድረስ ባሉ መዋቅሮች በመለየት ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል የውሃ መውረጃ ቦዮችን የመክፈትና ተያያዥነት ያላቸው ተግባራት እንደሚገኙበት ገልጸዋል። ለአብነትም በከፍተኛ ሁኔታ የስጋት አካባቢዎች ከሆኑት መካከል ሃላባ ዞን፣ ጉራጌ ዞን (ማረቆና ምስራቅ መስቃን ወረዳዎች)፣ ስልጤ ዞን ቆላማ ወረዳዎች፣ ሀዲያ ዞን ሻሾጎና ብላቴ ተፋሰስ፣ ወላይታ ዞን አበላ አባያ እንደሚገኙበት አመልክተዋል። በተጨማሪም በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋና ሳውላ ከተማ፣ ጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ፣ ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ የስጋት ተጋላጭ ተብለው መለየታቸውን ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል። የአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ለአደጋ እንዳይጋለጡ ማድረግና የውሃ መውረጃ መስመሮች በቆሻሻ እንዳይደፈኑ እየተሰራ እንደሆነ አመልክተዋል። የቅድመ መከላከል ሥራዎቹ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በከፍተኛ ንቅናቄ በመሰራት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። በክልሉ በሚገኙ ደጋማ ወረዳዎች የመሬት ናዳ የሚከሰትባቸው አካባቢዎች መለየታቸውንም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። ለአብነትም በጋሞ ዞን ገረሴ፣ ዲታ፣ ጨንቻ፣ ቦንኬ፣ ጋጮ ባባ፣ ዳራማሎና ካምባ ወረዳዎች ከፍታ ቦታዎች በዝናብ ወቅት ለናዳ ተጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በጎፋ ዞን መሎ ኮዛና ገዜ ጎፋ ወረዳዎች፣ ደቡብ ኦሞ ዞን ደቡብና ሰሜን አሪ ወረዳዎች፣ ወላይታ ዞን ኪንዶ ዲዳዬ፣ ካዎና ኪንዶ ኮይሻ ወረዳዎች ነዋሪዎችን በማውጣት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን አቶ ጋንታ አብራርተዋል። የክልሉ መንግስት የጎርፍ አደጋን ስጋት ለመቀነስ በመደበው በጀት ከ90 ኪሎ ሜትር በላይ የውሃ ማፋሰሻ ቦዮች መስራት መጀመሩን ገልጸዋል። በዚህም አስከፊ ችግሮች የሚከሰትባቸው አካባቢዎችን ከአደጋው መታደግ እንደተቻለ የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የጎርፍና ናዳ አደጋዎች በድንገት የሚመጡ በመሆናቸው አስጊ በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉም ጠቁመዋል። አቶ ጋንታ አክለውም በተለይም ወራጅ ወንዞች በድንገት በሚጥል ዝናብ ጉዳት እንዳያስከትሉ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል። የበልግ ዝናብ እየተካሄደ ላለው የግብርና ስራ ወሳኝ በመሆኑ ማህበረሰቡ ራሱን ከአደጋ እየተከላከለ ውሃውን በጥንቃቄ ወደ ማሳ በማስገባት ስኬታማ ለመሆን እንዲሰራና የደረሱ ሰብሎችን ፈጥኖ እንዲያነሳም መልዕክት አስተላልፈዋል።    
በአማራ ክልል  ዘንድሮ 316 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ  መከናወኑን  የግብርና ቢሮ አስታወቀ 
Mar 18, 2023 196
ባህር ዳር፤ መጋቢት 9 /2015 ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማጠናከር በዘንድሮው የበጋ ወራት 316 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ መከናወኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ስራው የተከናወነው በስምንት ሺህ 585 ተፋሰሶች ውስጥ መሆኑን ቢሮው ገልጿል። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ እስመላለም ምህረት ለኢዜአ እንዳመለከቱት፤ ከጥር ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከተከናወነው ስራ በ311 ሺህ 263 ሄክታር መሬት ላይ የማሳና የጋራ እርከን ይገኝበታል። እንዲሁም አራት ሺህ 813 ሄክታር የቦረቦር ልማትና አራት ሚሊዮን 893 ሺህ አነስተኛ የውሃ ማስረጊያ "ስትራክቸሮች" መሰራታቸውንም ገልጸዋል። በተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራው ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በመሳተፍ በበጋ ወራ ለማከናወን የተያዘውን እቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካት መቻሉን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። የተሰሩ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ዘላቂነታቸውን ለማረጋገጥ 7ሺህ 100 የተፋሰስ ልማት ህብረት ስራ ማህበራት ለማቋቋም ታቅዶ 2ሺህ 284 በማቋቋም ህጋዊ እውቅና አግኝተው ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቅሰዋል። ቀሪዎቹን ማህበራት እስከ መጪው ግንቦት ወር መጨረሻ አቋቁሞ ለማጠናቀቅ የሚያስችል የተጠናከረ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። የተፋሰስ ልማት ህብረት ስራ ማህበራቱም ተፋሰሶቹ በዘላቂነት ተጠብቀው ምርትና ምርታማነትን እንዲያሳድጉ ከማድረግ ባለፈ ዋነኛ የእንስሳት መኖ መገኛ ምንጭ እንዲሆኑ እንደሚያደርጉ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ የጋፍቲ ጉንካን ቀበሌ አርሶ አደር አንማው ጋሻዬ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት 12 ዓመታት ባከናወኑት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራም የአፈር መሸርሸር እየቀነሰ እንዲመጣ ማስቻሉን ገልጸዋል። የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ከመጀመራችን በፊት መሬቱ ለምነቱን ከማጣቱ የተነሳ በሄክታር እስከ 8 ኩንታል እናገኝ የነበረው ምርት አሁን እስከ 15 ኩንታል እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል። በዚሁ ዞን ደንበጫ ወረዳ የእግዚአብሄር አብ ቀበሌ አርሶ አደር አብራራው ፈንቴ ፤ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ጠንክረን መስራታችን የመሬቱ የአፈር ለምነት እየጨመረ እንዲመጣ አድርጓል ሲሉ ገልጸዋል። በቀጣይም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ ያለማንም ቀስቃሽ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት በአርሶ አደሩ ተሳትፎ 295 ሺህ 364 ሄክታር መሬት ላይ የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ መከናወኑ ከግብርና ቢሮው የተገኘው መረጃ ያሳያል።  
 በጋምቤላ ክልል አምስተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ ልማት 12  ሚሊዮን የሚጠጉ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው - የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ
Mar 17, 2023 226
ጋምቤላ መጋቢት 8/2015 (ኢዜአ) በጋምቤላ ክልል በአምስተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ ልማት 12 ሚሊዮን የሚጠጉ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ ባለፈው የክረምት ወቅት ከተተከሉት 10 ሚሊዮን ችግኞች መካከል "85 መቶ የሚሆነው መጽደቁን" ገልጿል። የጋምቤላ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ኃላፊ አቶ አጃክ ኡቻላ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በክልሉ የአካባቢ ልማትና ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር ምርታማነትን ለማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው። በተያዘው የበጋ ወራትም ከ60 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ የተራቆተና የእርሻ መሬት ላይ ሕብረተሰቡን ያሳተፈ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። በበጋው ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ እና ልማት የተካሄደባቸው አካባቢዎችን በአምስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሐግብር በችግኝ ለማልበስ ታቅዷል ብለዋል። አካባቢዎቹን በስነ-ህይወታዊ ዘዴ ለማልበስም በክልሉ በሚገኙ 104 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች 11 ነጥብ 75 ሚሊዮን ችግኞችን የማዘጋጀት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ነው አቶ አጃክ የጠቆሙት። ችግኞቹ የፍራፍሬ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው መሆናቸውንም በመግለጽ። በተያያዘም "በክልሉ ባለፈው የክረምት ወቅት ከተተከሉት 10 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መካከል 85 በመቶ የሚሆነው ጸድቋል" ነው ያሉት የቢሮ ኃላፊው። የጋምቤላ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ባለሙያ አቶ ቻም ኡራሚ በበኩላቸው፣ በ2014 የክረምት ወቅት ሕብረተሰቡን በማሳተፍ በተከናወነ የእንክብካቤ ስራ በአንዳንድ አካባቢዎች ሁሉም ሊባል በሚችል ደረጀ ችግኞቹ መጽደቀቻውን ተናግረዋል። በሌላ በኩል የበጋውን ሞቃታማ የአየር ጸባይ ተከትሎ ሊከሰት የሚችለውን የሰደድ እሳት ለመከላከል በተከናወኑት የሰደድ እሳት መከላከያ እርከን ስራዎችም ይደረስ የነበረን ቃጠሎ መቀነስ መቻሉን አመልክተዋል። በጋምቤላ ከተማ በከተማ ግብርና ሥራ ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል ወጣት ሙኒር ኢሳ በሰጠው አስተያየት፣ አሁን ላይ ከግብርና ልማት በተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሚታ ያላቸውን ችግኞች በማልማትና በመትከል ተጠቃሚ መሆን መጀመሩን ገልጿል። በተለይ ከጓሮ አትክልት በተጨማሪ ፓፓያ፣ ማንጎ፣ ሎሚ፣ ብርቱካንና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሚታ ያላቸውን ችግኞች በማልማት በምግብ እራስን ለመቻል እየሰራ መሆኑን ተናግሯል።  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 449
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተገለጸ
Dec 20, 2022 458
አዲስ አበባ ታኅሳስ 11/2015 (ኢዜአ) አህጉራዊው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፍሪካ ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተመላከተ። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ከአፍሪካ ጋር ያላት የንግድ ትስስር ከባህረ-ሰላጤው ሃገራት መካከል በቀዳሚነት እንደሚጠቀስም ተገልጿል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዊሊያም ስቴንሀውስ ከሲ ጂ ቲ ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በተለይም ዱባይ የአፍሪካን ንግድና ኢንቨስትመንት በተመለከተ ዋና ማዕከል ሆናለች ብለዋል። በዱባይ 25ሺህ ገደማ የአፍሪካ ካምፓኒዎች እንደሚንቀሳቀሱ አመልክተው ይህም ሀገሪቱ በነጻ የንግድ ቀጣናው የቢዝነስ አጋር እንድትሆን አስችሏታል ነው ያሉት። አፍሪካውያን ባለሃብቶች የግብይት ማዕከላቸውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በማድረግና ምርቶችን ወደ አህጉሪቷ በማስገባት በነጻ ንግድ ቀጣናው ስር የገልፍ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደጉት እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የዱባይ ወደብ በአፍሪካ ያለው ተደራሽነት መስፋፋትም አፍሪካ ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የሎጀስቲክስ አቅርቦት እንደሚያሳድግ በመረጃው ተመላክቷል። ከገልፍ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት ከኢኮኖሚያዊ ትስስር ባለፈ ዲፕሎማሲያዊና ወንድማማችነትን መሠረት ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬት የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ናቸው። አምባሳደሩ እንደሚሉት ከመካከለኛው ምስራቅ መነሻቸውን ያደረጉ ባለሃብቶችና የቢዝነስ ሰዎች ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋር በልዩ ልዩ ዘርፎች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ይገኛል። እ.አ.አ በጥር 2021 ተግባራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ከአጀንዳ 2063 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቱን ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም የዲጂታል ንግድ፣ የኢንቨስትመንት ትስስርና ሌሎች የንግድ ግንኙነቶችን በነጻ የንግድ ቀጣና ለማከናውን የተካሄደ ስምምነት ነው።
ሐተታዎች
ውጣ ውረድ የማይበግረው አጋርነት
Mar 17, 2023 201
በሰለሞን ተሰራ ኢትዮጵያ በሥልጣኔ ቀደምትና ታሪካዊት ሀገር ነች። ቅሉ ከውጭ ሀገራት ያላትን ዘመናዊው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቅኝት የጀመረችው በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑ በታሪክ ይጠቀሳል። በተለይም ኢጣሊያ በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1896 በአድዋ እንዲሁም በድጋሚ በ1935 ያደረገችው የግፍ ወረራ ኢትዮጵያ የዓለምን ፖለቲካ በቅጡ አሰላለፍ ተረድታ አጋር ሀገራትን እንድትሻ ዐይኗን ገልጦላታል። በዚህም ድኅረ-አድዋ ድል በርካታ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መስርተዋል። የወቅቱ ልዕለ-ኃያል ሀገር አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷ የተመሰረተውም በዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና በፕሬዝዳንት ሩዝቬልት መንግሥት ተወካይ ሮበርት ስኪነር መካከል በፈረንጆቹ አቆጣጠር 1903 በተደረሰው የንግድ አጋርነት ስምምነት ነበር። ድኅረ-ስምምነቱም በፈረንጆቹ በ1909 የአሜሪካ ሌጋሲዮን በአዲስ አበባ የተመሰረተ ሲሆን ሆፍማን ፊሊፕ የተባሉት ቋሚ መልዕክተኛ የአሜሪካ ቆንስላ ተሿሚ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአፄ ምኒልክ አቅርበዋል፡፡ ከ120 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የኢትዮ-አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በጽኑ ወዳጅነትና የጋራ ጥቅሞች ላይ የተመሰረተ እንደነበር ይወሳል፡፡ ሀገራቱ ጥቅማቸውን በጠበቀ መልኩ የመሰረቱት ግንኙነት ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማምጣት ታሳቢ ያደረገ መሆኑም አይዘነጋም፡፡ የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራን ተከትሎ ቆንስላዋን የዘጋችው አሜሪካ፤ ኢትዮጵያ በአርበኞቿ ትግል ነፃነቷን ስታረጋግጥ በፈረንጆቹ አቆጣጠር በነኅሴ 1943 በድጋሚ ቆንስላዋን በመክፈት ግንኙነቷን አስቀጥላለች። በተመሳሳይ ወቅት ኢትዮጵያ በአሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የቆንስላ ቢሮ ከፍታ ዕውቁን ዲፕሎማት ብላታ ኤፍሬም ተወልደመድኅንን በቋሚ መልዕክተኛነት ሾማለች። በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1952 የተደረገው 'ፖይንት ፎር' የተሰኘው የተቋማት ቴክኒክ ድጋፍ ስምምነት ለሁለቱ ወዳጅ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ይበልጥ መሰረት የጣለ እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ በዚህ ስምምነትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የአውራ ጎዳና ባለሥልጣን እና የኢትዮጵያ ካርታ ሥራ ድርጅት በአሜሪካ መንግሥት ድጋፍ ተቋቁመዋል። የሁለትዮሽ ግንኙነቱ አድማሱን እያሰፋ፣ ሥር እየሰደደ ቀጥሎ ኢትዮጵያ ጦር ሠራዊቷን እንድታጠናክር በአነስተኛ የጦር መሳሪያዎች፣ ተሽከርካሪዎችና ወታደራዊ ሥልጠናዎች ተጨባጭ አጋርነት አሳይታለች። የደርግ ወታደራዊ መንግሥት ሥልጣን በተቆጣጠረ ማግስት ግን በዘመኑ በነበረው ዓለም አቀፋዊ ርዕዮተ- ዓለም ልዩነት ሳቢያ የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሻክሮ ሌላ መልክ ያዘ። በተለይም የደርግ ሊቀ-መንበር የነበሩት ሌተናል ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ወደ ሶቪየት ሕብረት አቅንተው የጦር መሳሪያ ድጋፍ መፈራረማቸው አለመግባባቱን ይበልጥ አባባሰው። በዚህም አሜሪካ በኤርትራ የነበረውን የቃኘው ሻለቃ ጣቢያዋን ዘግታ ወጣች። ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ከአምባሳደር ደረጃ በማውረድ በጉዳይ አስፈጻሚ ሲገናኙ ቆይተዋል፡፡ ኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን ሲመጣ የሀገራቱ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ቀድሞ ወደነበረበት የአምባሳደር ደረጃ በመመለስ ከአሜሪካ ጋር የነበረው ግንኙነት መልሶ እንዲያንሰራራ አድርጎታል፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት አሜሪካ በጤና፣ በሰብዓዊ ድጋፍ፣ በመልካም አስተዳደርና በዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ላይ በምታደረገው ድጋፍ በመታገዝ በጋራ ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ ከሦስት ዓመታት ወዲህ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ አሜሪካ መርህን ያልተከተለ አካሄድ በሀገራቱ መካከል የነበረውን ወዳጅነትና አጋርነት ላይ ጥቁር ጥላ ማጥላቱ አይዘነጋም፡፡ ነገር ግን ባለፉት ሦስት ዓመታት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ሻክሮ የቆየውን ግንኙነት በማደስ የነበረውን ጠንካራ ወዳጅነት በድጋሚ የሚያጸኑ ጅማሮዎች ተስተውለዋል። በተለይም ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የተደረሰውን የሰላም ሰምምነት ተከትሎ የሀገራቱ መቃቃር እየረገበ ሲሆን የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ኢትዮጵያን በተደጋጋሚ እየጎበኙ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ከትናንት በስቲያ አዲስ አበባ የገቡት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፤ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ተነጋግረዋል። አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ያደረጉት ውይይት ዘርፈ-ብዙ አጋርነትን ለማጠናከር መግባባት የተደረሰበት እንደነበርም በሁለቱም ወገኖች ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ውይይቱ በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደሆነና በኢትዮጵያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ስምምነት የተደረሰበት እንደሆነ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት ማግኘቱንም ጠቅሰዋል። በኢኮኖሚው መስክ በተለይም በግብርና እና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ባተኮሩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት መነጋገራቸውን በመልዕክታቸው ጠቁመዋል። በተመሳሳይ አንቶኒ ብሊንከን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ባደረጉት በሁለትዮሽና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በትኩረት መክረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ሚኒስትሮቹ ለረዥም ዘመን የዘለቀውን የኢትዮ-አሜሪካ ትብብር እና አጋርነት ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ተነጋግረዋል። በኢትዮጵያ አዲስ የመረጋጋትና የሰላም ምዕራፍ መከፈቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን አብራርተውላቸዋል። የሰላም ምዕራፍ የበለጠ እንዲጠናከርና የሰመረ እንዲሆን ከዚህ ባለፈም የሀገሪቱን በጎ ገጽታ እንዲላበስ መንግሥት በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ እምርታ እንዲመጣ ለሰላም ስምምነቱ ተፈፃሚነት መንግሥት አሁንም ቁርጠኛና ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ጠቅሰው፤ በመልሶ ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም ተግባር የአሜሪካ መንግሥት እንዲደግፍም ጠይቀዋል፡፡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በበኩላቸው፤ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሻገር አሜሪካ በትብብር መንፈስ እንደምትሰራ እና አሜሪካ ሁለንተናዊ ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። አሜሪካ ለድርቅ ተጎጂዎች እና ለስደተኞች የምታደርገው ድጋፍ አለመቋረጡ የሁለቱ ሀገራት አብሮነት ተጠናክሮ መቀጠሉን ይጠቁማል፡፡ የብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝት ከኢትዮጵያ መጀመሩም ዛሬም ኢትዮጵያ በአሜሪካ መንግሥት ዐይን ያላትን ቀዳሚ ሥፍራ ያመለክታል። አንቶኒ ብሊንከን የሰላም ትግበራ ሂደቱ በመልካም ሁኔታ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ የበለጠ እንዲጠናከር የአሜሪካ መንግሥት ሁለገብ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የሁለቱን ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆኑን ማረጋገጡን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ እያደረገች ያለውን ጥረት አሜሪካ በአድናቆት እንደምትመለከተውና የሚበረታታ መሆኑን ብሊንከን ገልጸዋል። የብሊንከንን ጉብኝት ተከትሎ አሜሪካ 331 ሚሊየን ዶላር ተጨማሪ የሰብዓዊ ድጋፍ ለኢትዮጵያ እንደምታደርግ አረጋግጣለች። ድጋፉም በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ወገኖች ነፍስ አድን ሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።  
የሴቶች ቀን ሲታሰብ
Mar 8, 2023 394
የሴቶች ቀን ሲታሰብ የሰው ልጅ ሕይወትን ቀላል ባደረጉ የፈጠራ ስራዎቻቸው የምናስባቸው እንስቶች በቀዳሚነት ይነሳሉ። በተለያዩ መስኮች አሻራቸውን ያሳረፉ እንስቶች ቁጥራቸው ከፍተኛ ቢሆንም በዚህ ጽሑፋችን ግን በኬሚስትሪና ፊዚክስ ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ ባበረከቱት አስተዋጽኦ በኖቤል ሽልማት እውቅና የተሰጣቸውን የየዘመኑ ፈርጦች እንዳስሳለን። ከነዚህ ፈርጦች መካከል በኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤልን ሽልማትን ከሴቶች ቀዳሚ በመሆን በቀዳሚነት ያሸነፉት ሜሪ ኩሪ ይወሳሉ። ይልቁንም እ.አ.አ በ1903 በኬሚስትሪ ዘርፍ የተቀበሉትን የኖቤል ሽልማት በድጋሚ በ1911 በመሸለም ብቸኛነት ስማቸው ይነሳል። በ1967 በፖላንድ ዋርሶ የተወለዱት ማሪ ኩሪ ለዘመናዊው የሳይንስና ኬሚስትሪ ዘርፍ ውለታን ከዋሉ ስመጥር ተመራማሪዎችና በጨረራ ህክምና ፈጠራ የዘርፉ ፈር ቀዳጅ በመሆን የአለምን የራዲዮአክቲቪቲ እይታን የቀየሩ ጀግና ናቸው።   የሜካኒካልና ኤሮስፔስ ተመራማሪዋ ፍራንሲስ አርኖልድ ደግሞ በህክምናናና በታዳሽ ኃይል ዘርፍ አሻረቸውን በጉልህ ካኖሩ ተመራማሪዎች መካከል ይጠቀሳሉ። አሜሪካዊቷ ፍራንሲስ ለታዳሽ ኃይል እና ለፋርማሲ አገልግሎት የሚውል አዲስ ኢንዛይም በምርምር በማግኘት በዘረፉ አሻራቸውን አኑረዋል። ለዚህም አስተዋጽኦዋ እ.አ.አ በ2018 በኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤልን ሽልማት አሸንፈዋል። የኤድስን ስርጭትን በመከላከል ረገድ ሰፊ አበርክቶ ያላቸው የህክምና ተመራማሪዋ ፍራንሶዝ ባሪሲኖሲም የሴቶች ቀን ሲታሰብ ከሚወሱ አንስቶች አንደኛዋ ናቸው። ባሪሲኖሲ የኤች አይቪ ኤድስን ከገዳይ በሽታነት መታከምና መቆጣጠር ወደ ሚችል በሽታነት ለመቀየር የኤች አይቪ ኤድስ ምርመራን በማላቅ ረገድ ሚናቸው የጎላ እንደሆነ ይወሳል። በ1947 በፓሪስ ከተማ የተወለዱት ባሪሲኖሲ “ሳይንስን ለሰው ልጆች ጥቅም እንዲውል እንሰራለን” በሚለው አባባላቸው ይታወቃሉ። ኤድስን በመከላከል ላደረጉት አስተዋጽኦም በፊዚዮሎጂ/ሕክምና ዘርፍ እ.አ.አ በ2008 የኖቤል ሽልማትን አግኝተዋል። ያለ ህክምና ትምህርት የሚሊዮኖችን ሕይወት በታደገው የወባ በሽታ መከላከያ ፈጠራቸው አለም እውቅና የተሰጣቸው ቱ ዩዩ በሴቶች ቀን የምናመሰግናቸው ሌላኛዋ ተመራማሪ ናቸው። ቻይናዊቷ ቱ ዩዩ ባህላዊውን የወባ በሽታ መከለከያ ህክምና ወደ ዘመናዊ በመቀየርና በማስተዋወቅ ነው ስመ ገናና የሆኑት።   የወባ በሽታን በመከላከል ረገድ በአለም አቀፍ ደረጃ ጉዙፍ አሻራቸውን ላስቀመጡት ተመራማሪ ባለውለታነት እ.አ.አ በ2015 በፊዚዎሎጂ/ ህክምና ዘርፍ ሳይንስ ምድብ የመጀመሪያዋ ቻይናዊት በመሆን የኖቤል ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የሰው ልጆችን ሕይወት ካቀለሉ አለም አቀፍ ፈጠራዎች መካከል የተጠቀሱትን ጨምሮ በሌሎችም ዘርፎች የሴቶች ተሳትፎ የጎላ መሆኑ ይታወቃል።
ሴትነት እና እናትነት
Mar 8, 2023 567
(አየለ ያረጋል) እስኪ መላ ስጪኝ መላ ካንቺ ይገኛል እኔማ ወንድ ነኝ ይደናገረኛል… (የማኅበረሰቡ ቃላዊ ግጥም) ሴትነት እናትነትን ለመግለጽ ቀርቶ በጥቂቱ ለመረዳት የ’እናት ልብ’ መታደል የሚሻ ይመስላል። ጥቂት ወንዶች ይህን ጸጋ ይቸራሉ። ልክ እንደ ዶክተር ይሁኔ አየለ። የስነ-ምግብ ሳይንቲስቱ ዶክተር ይሁኔ አየለ ‘እናት’ በሚል ርዕስ ባሳተሙት ድንቅ መጽሐፍ የሴትነት እና እናትነትን ከፍታ በ’ኩርሽም’ ቃላት ተራቀውበታል። የሴቶች ቀንን (ማርች-8) ሰበብ በማድረግ ይህን ጽሑፍ ሳዘጋጅ መታሰቢያነቱ እናትን አስበው በ‘እናትነት’ ቅን ልቦና ‘እናትን’ ላበረከቱልን ዶክተር ይሁኔ አየለ ነው። ‘እናት፤ የሴት ልጅ ስንክሳር፤ ከቤተሰባዊ ሕይወት እስከ ሐልዮመንበርት’ በሚል ርዕስ በቅርቡ ባሳተሙት (በ406 ገፆች በተቀነበበ) አርበ ጠባብ መጽሐፍ ሴትነትን ከዘፍጥረት እስከ አሁን ዘመናትን ዋጅተው፣ እናትነትን ከሴትነት ዘንቀው፣ የእናትነት ጸጋን ከነባራዊ ሃቅ ጋር አሰነናስለው፣ የእናትነትን ልዕለ-ተፈጥሮ አርቅቀው፣ የዓለምን ክብር-ነሽነት ከነገረ-ሃይማኖት እስከ ነገረ-ባህልና ፍልስፍና ፈትተው፣ የማኅበረሰቡን ምልከታ ዝንፈት እና ሚዛን ጉድለት ከማኅበራዊ እስከ ፖለቲካዊ መገለጫዎች አዛምደው አቅርበውታል። ዶክተር ይሁኔ አየለ “እናት” በተሰኘ እናት የሆነ መጽሐፋቸው እናትነትን በልኩ ነጽረውታል። ሴትነት በኢትዮጵያ የአስተሳሰብ ሰለባነቱን፣ ነገረ-ሴትነትን ከንጽረተ-ሴትነት ቃኝተውታል። በእሳቤ ሚዛን ሰለባነት ዓለም ውስጥ ከንግስት ማክዳ እስከ ንግስት ፉራ፣ ከሰብለ ወንጌል እስከ ድል ወንበራ፣ … ብርቱ ኢትዮጵያዊት ሴቶችን ሕይወት ጨልፈውታል። የሴትነትን ጸጋዎች ጨልፈው በሴትነት ላይ የሚፈጸሙ የሀበሻ ግፎችን ተንትነውበታል። ሴቶች የማኅበረሰቡ ግፍ ሰለባዎች፣ የማኅበራዊ ፍትህ ጉድለት ሰለባዎች እንደሆኑ በቅጡ ገልጸውታል። ዳሩ ሴትነት ጀግና እና ብልህ፣ የቤተሰብ መሰረት፣ የደስታና እልልታ እናት፣ ቃል ኪዳንና ክብር ጠባቂ እንደሆነ ገልጸዋል። “ሴት ልጅ ባለብዙ ጸጋዎች ናት። ከጸጋዎቿ መካከል ጀግንነት እና ብልሃት ይጠቀሳሉ። … ሴት ልጅ ባህልን ፈጥራ የማኅበራዊነትን ማስተሳሰሪያ ገመዶች ገምዳ አስተሳስራ ማኅበረሰብን የተከለች ሥርዓት ናት። … ቤተሰብ የአንድ ማኅበረሰብ የመጀመሪያ ተቋም ነው። የተቋሙ ባለሥልጣን (እመቤት) ሴት ናት። ያቺ ሴት እናት ናት። ቤተሰብ የስብዕና መሰረት የሚባለው እናትን ምሰሶ አድርጎ ነው” (ገጽ-285) ሴት ልጅ መለኛ መሆኗን ማኅበረሰባችን ቢያምንም ሴትነትን ግን እንዳላከበረ አሉታዊ ይትባህልና ኪነተ- ቃሉን ዘይቤ ያወሳሉ። በእርግጥ የእናትን ምቹነት እና ዋጋ ከፋይነት የሚያትቱ የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎችም አሉ። ለምሳሌ ዳንኤል አበራ “የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎች” በሚለው መጽሐፋቸው “እናት ትረገጣለች እንደመሬት፤ እናት ለልጄ ልጅ ለነገዬ፤ እናቷን አይተህ ልጅቷን አግባ፤ እናት የሌለው ልጅ እንደ ጌሾ፤ ሳይበላ የበላ ሳይናገር ዋሾ…” የሚሉ ምሳሌያዊ ንግግሮችን አስፍረዋል። መላኩ ይርዳው የተባሉ ጸሐፊ ‘ደቦ ቅጽ-፩’ ከተሰኘው የ60 ደራሲያን ሥራዎችን ያካተተ መጽሐፍ ውስጥ ‘የሴትነት ጸጋ’ በሚል በጻፉት መጣጥፍ ሴትነትን ከፍቅር፣ ከጥበብ፣ ከብልሃትና ልዕልና ጋር አቆራኝተውታል። “ሴት ልጅ ቅኔ ናት፤ ከተባለላት፣ ከተጻፈላት፣ ከተዜመላት በላይ የረቀቀች ረቂቅ ቅኔ ናት። እስከዛሬ ከያኒያን ስለሴት ከተራቀቁት፣ ከተጠበቡት ሁሉ እኔ ለማውቃት ሴት ሁሉ የሚመጥኑ ሆነው አልታዩኝም። የሴትነት ጸጋው ብዙ ነውና የሴትን ትክክለኛ ማንነት መርምረን አጥንተን የደረስንበት ውስጠ-ስሪቷን አጥንተን የተረዳነው አይመስለኝም።… ከታላቅነቷ፣ ከብልሃቷ፣ ከረቂቅነቷ፣ ከመግዛት አቅሟ፣ ከርህራሄዋ፣ ከሰላማዊነቷ ከሌሎችም አያሌ በረከቶች አንጻር ለሴት ልጅ የተደረገላት፣ የተነገረላትና የሆነላት ሁሉ ያንስብኛል” ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) ስለሴት ልጅ ጭቆና የታገለ እና ስለክብሯ የዘመረ ምሁር ነው። ስለሴት ልጅ ስቃይና ሰቆቃ አትቷል። ‘በናቴኮ ሴት ነኝ’ በሚለው መጽሐፉ ስንኞች እንምዘዝ! …. ግማሽ አካሏ ወንድ በትምክህት ቢከዳት ጧ! ብላ አለቀሰች አዛኝ ቢደርስላት፣ … ብሶት ተጫጭኗት ምንም ሰው አልሆነች በቀቢጸ ተስፋ ሕላዌንም ጠላች ያገሬ ጭቁን ሴት መድኅን መላ ያጣች….! ‘ሔዋንያት የትውልድ ፋብሪካዎች ናቸው፤ እነሱ ባይኖሩ ዓለም ባዶ ትሆን ነበር’ እንዲል ፈላስፋው ሶቅራጥስ። ስለሴት (ግማደ ሰቧ ፍጡር) ግፍና በደል ገሞራው እንዲህ ይላል። “መራራ ጭቆና በሰፈነበት ምዝብር ሕብረተሰብ ውስጥ ታፍነው የሚኖሩ ሔዋንያት ብሶታቸው፣ ፍዳቸው፣ በደላቸው፣ ጭንቀታቸውና መከራቸው እንደ ሰማዕታት ገድል እጥፍ ድርብ ነው…. አጉል ልማድ፣ ኋላቀር ባሕልና አድሃሪ ሕገ-ማኅበረሰብ ከከንቱ አስተሳሰቦች ጋር ተዳምሮ በአንድነት በመመሳጠር ዘርዓ ሔዋንን ሲጫወቱባቸው ሲያሾፉባቸው ኑረዋል” (ገጽ-23) በሥነ-ሕይወት ሳይንስና በትምህርተ-ጄነቲክስ (አካለ ሕላዌ) ሴቶችን ከወንዶች የሚያሳንስ ምንም አይነት አካላዊ ተሰጥኦ እንደሌለ ተረጋግጧል። ታሪክና ተረክ ግን ወገንተኛ መሆኑን ገሞራው ይናገራል። ተረክና ተረት አልባሌ ታሪክ የሚፈጥሯቸው አርበኞች ሁሉ በፆታቸው ተባዕት በመሆናቸው፤ በሴቶች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ በማሳደሩ ሊኖራቸው የሚችለው ዕድገት ላይ ትልቅ ደንቃራ ሆኖ መቆየቱን ይገልጻል። “የታሪክን ሁኔታዎችን የመመንዘር ትርጓሜያዊ አንጻር የታሪክን ትዕይንቶች ብንመረምር አንደርድሮ የሚያደርሰን ሴቶች ከወንዶች የከፋ ባህሪያዊ ድክመት እንዳለባቸው ከሚያሳይ ሥዕል ላይ ነው።” በሚት(ተለጣጭ ተረክ) ላይ የሚራቀቁት አቶ ቴዎድሮስ ገብሬ (በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፎክለር መምህር) ‘ተረኮች እማዊ ሳይሆን አባዊ ናቸው’ በማለት ይህን ጉዳይ ያጠናክሩታል። “በሚት ውስጥ ገነው ከሚታዩ አበይት ማኅበራዊና ባህላዊ እውነታዎች መሃል አንዱ ፆታዊ ወገንተኝነት ነው። የሰማናቸው፣ ያነበብናቸው ሚታዊ ተረኮች በእጅጉ አባዊ ለሆኑ ሥርዓቶች (ፓትሪያርካል ሲስተምስ) ያደሩ፣ በአብዛኛው በተባዕት ተጋዳሊያን የተሞሉ ናቸው” ይላል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዶክተር ይሁኔ (በገፅ-401) ስለሰው ማንነት ቀረጻ በተመለከተ ከጥንት እስከ ዛሬ አከራካሪ የሆኑ ፈላስፎችን ክርክር ያነሳሉ። ይኸውም የሰው ልጅ ‘ማን ቀረጸኝ? ተፈጥሮ ወይስ ተሞክሮ?’ የሚለውን መከራከሪያ ጽንሰ-ሃሳብ ይፈትሻሉ። በዚህም “ሰዎች ሲፈጠሩ የሰውየውን ችሎታ ይዘው ነው” እና “የሰዎች ማንነት የሚቀረጸው ከውልደት በኋላ በተሞክሮ ወይም ከአካባቢ ጋር በሚኖራቸው መስተጋብር ነው” የሚሉትን ሃሳቦች ወስደው ከእናት ሚና ጋር ያዛምዱታል። እናም እናት ‘በየትኛውም መደብ ልጅን አሳምራ ትቀርጻለች’ የሚል ድምዳሜ ሰጥተዋል። “በየትኛውም መንገድ በሰው ልጅ ላይ የእናት ቀራፂነት ስለሚኖር ከተጽዕኖዋ ማምለጥ የሚቻል አይመስለኝም።… አካባቢም ሰውን ይሰራዋል የሚሉትም ከውልደት በፊትም ሆነ በኋላ ከተፈጥሮ ጋር የሚደረገው ውስብስብ መስተጋብር ‘ሰው’ በመሆን ላይ ጉልህ ሚና ይጫወታል” ይላሉ። በዚህ እሳቤ ሰው የወላጆቹም፤ የአካባቢውም ውጤት መሆኑን በግልጽ እንረዳለን” ይላሉ። ሴቶች ከጥንት እስከ ዛሬ በኢትዮጵያ ማኅበረ-ባህላዊ እንዲሁም ለሰላምና ዕርቅ እሴቶች ጉልህ ሚና አላቸው። ሴቶች ያልተሳተፉበት ዘርፍ የለም። ከመሪነት፣ ጥበበኝነት፣ ከአገር ድንበር ጠባቂነትና የዲፕሎማሲያዊ ሚና… መጥቀስ ይቻላል። ሴቶች በሁሉም ማኅበረሰብ ዘንድ በሰላምና ግጭት አፈታት ግንባር ቀደም ተሰሚነት አላቸው። ለአብነትም ሀደ ሲንቄ፣ በሶማሌ-ሔር፣ በሲዳማ-ያካ፣ በራያ ማኅበረሰብ ዱበርቲዎች፣ በስልጤ-ሴረን ባህል መጥቀስ ይቻላል። ከሰሞኑ ባከበርነው የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ሴቶች ውለታ በወፍ በረር ማውሳት ይቻላል። የኢትዮጵያ ሴቶች ከሌላው ዓለም ሴቶች በተለየ የራሳቸው ቀለም ያላቸው፣ የአመራር ልምድ ያዳበሩ፣ የመወዳደሪያ ስነ-ልቦና ያላቸው፣ ችለው አሸንፈው ያሳዩ ናቸው። ሴቶች ድሉን በማስመዝገብ የተጫወቱትን ሚና ያህል፣ ገድላቸው በታሪክ በሚገባ አልተወሳም። ዶክተር አልማው ክፍሌ የተባሉ የታሪክ ምሁር በአንድ ወቅት ሚዲያ ላይ ቀርበው “በአድዋ ጦርነት ዘማቾች 75 በመቶ ሴቶች ነበሩ” ሲሉ ሰምቻለሁ። በአድዋ ጦርነት ሴቶች በተለያዩ ሙያዎች ተመድበው ከካምፕ እስከ ጦር ሜዳ ከመመገብ እስከ ማጀገን፣ ከማከም እስከ መዋጋት ድንቅ ሚና ተወጥተዋል። ድርብ ድርብርብ ኃላፊነት ይዘው የዘመቱ፣ ለወንዶችም ልብ፣ ሞራልና ወኔ አቀባዮች ነበሩ። እቴጌ ጣይቱን መሰል የአድዋ ሴት የጦር ፊታውራሪዎች በርካታ ናቸው። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ ወልደአረጋይ ‘ታሪክ ዘመን ዘዳግማዊ ምኒልክ’ በተሰኘው መጽሐፋቸው የሴቶችን ሚና በተመለከተ እንዲህ ይላሉ፡- “እንዲህም እየሆነ፣ አጤ ምኒልክ ባዳራሹ እቴጌ ጣይቱ በእልፍኝ ባለሟሎችዎን ወይዛዝርቱን ይዘው ግብሩ አንድ ቀን ሳይጎድል፣ ይዘምታሉ። ከዘመቻ ላይ ጠጁ ማሩ አለመጉደሉ፣ ስለምንድነው ያልህ እንደሆነ ይህን ታሪክ መመልከት ነው። በስድስት ድንኳን እንጀራው ሲጋገር ሲያድር፣ በአራት ድንኳን ወጡ ሲሠራ ሲያድር፣ ጠጁ በቀንድ በኮዳ ደግሞ ሦስት መቶ ስድስት መቶ የሚሆን ገንቦኛ ሲጓዝ ግብሩ ይጎድል ይመስልሀል” (ገጽ-241) ደራሲ በዕውቀቱ ሥዩም ‘ከአሜን ባሻገር’ በተሰኘ መጽሐፉ ‘ሴቶች በዋሉበት’ በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ሴቶች ተጋድሎና ሚና “ከቁስ ባሻገር ከልብ ያቀርባሉ” ይላቸዋል። “ሴቶች ባዋላጅነት ከነበራቸው የማይተናነስ ሚና በጦር ሜዳ ተጫውተዋል። እናቶቻችን በጦር ወቅት፣ መሳሪያ ያቀርቡ ነበር። ምግብ ያቀርቡ ነበር። ሃሳብ ያቀርቡ ነበር። ልብ ያቀርቡ ነበር። ደስታ ያቀርቡ ነበር። ኧረ ምኑ ቅጡ። ሴቶች ባንድ በሙቀጫ ዙሪያ፣ ማኅበረሰቡን ኬሚስት፣ ገጣሚና የፖለቲካ ተንታኝ ሆነው ማገልገላቸውን ልብ እንበል” ይላል። (ገጽ-138) ዶክተር ይሁኔ (በገጽ-14) በበኩላቸው እናቶችን ሩህሩሆች፣ አጉራሽና አልባሽ፣ የችግር ቤዛዎች፣ ሕይወት ዑደት አስቀጣዮች፣ የሕይወት መድኅኖች፣ ባለብዙ ጸጋዎች፣ መልካም ባህሪ አውራሾች፣… በማለት ገልጸውታል። መላ ሴቶችንም በእናቶች አተያይ ማየት እንደሚገባም እንዲሁ። “እናትነት መልካም ገጽታዎችን ደራርቦ የያዘ የሴት ልጅ ትልቅ መገለጫ ነው። እናትነት ከፍ ያለ ሥልጣን ነው። እናትነት ጥልቅና ሰናይ ባህሪያት የሚፈልቁበት ምንጭ ነው። እናትነት የደግነት፣ የጥራት፣ የልህቀትና ተፈላጊነት ማሳያ ተምሳሌት ነው። እናትነት ሞት የማያደበዝዘው ኃያል መንፈስ ነው። እናትነት ከባድ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነው። … እናትነት የሰላም፣ የመልካም ግንኙነትና እንክብካቤ መፍለቂያ አድባር ናት። እናትነት ሰፊና ጥልቅ የሕይወት ትምህርት ቤት ነው። እናትነት ሌሎች ከስቃይ ነፃ እንዲሆኑ፣ ምቾት እንዲሰማቸው በሚደረግ ትግል ውስጥ ዋጋ እየከፈሉ መኖር ነው” በመቀጠልም የኢትዮጵያ እናቶችን ‘ጠቃሚ ነገር ሰጪዎች’ ይላቸዋል። “እናቶች ሰው የመሆኛ ቅመሞች የሚጨለፍባቸው ባህር ናቸው። … ሕይወታዊ ስሪታችን ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን የወሰደው ከእናት ነው። ከእናት የምናገኘው ‘ማይቶኮንድሪያ’ (ማይቶኮንድሪያ የኃይል ማመንጫ ክፍል ሲሆን የምንመገበው ምግብ እየተቃጠለና ወደ አስፈላጊው ኃይል እየተቀየረ ሕይወትን ያንቀሳቅሳል) የምግብ ማቃጠያ ምድጃ ወይም ኃይል ማመንጫ ቤት ሆኖ ያገለግላል። … ብዙ መልካም ስብዕና መገለጫዎች ምንጫቸው የእናት ፍቅር፣ የመልካም ስብዕና እና የርህራሄ ምንጭ ነው” (ገጽ- 61) ኢያሱ በካፋ ‘የኢያሱ በካፋ ወጎች’ በተሰኘው መጽሐፉ እናትነትን ማህጸንን፣ ምግብን፣ ትንፋሽን፣ ደም፣ ሥጋን እና ነፍስን ሰጥተው በረቂቅ ተፈጥሮ ሰውን ከመውለድ ባለፈ ፍቅራቸውን ዘላለማዊ ገደብ አልባ እና ዕልቆ-ቢስ እንደሆነ እንዲህ ገልጾታል። “እናትነት ነፍስን ማካፈል ነው፤ እናትነት የማይደበዝዝ ዘላለማዊ ፍቅር መስጠት ነው፤ እናትነት ከራስ ሕልውና ይበልጥ ለልጅ ማሰብ ነው፤ እናትነት ፍፁም ወረት አልባ መሆን ነው። እናት ለልጇ ያላት ፍቅር አይነጥፍም፤ አይለወጥም። ለእናት ልጇ ሁሌም ልጇ ነው” (ገጽ-4) እናትነት በቃላት ለመግለጽ እንደሚከብድ፤ በውለታ ማካካስ ይከብዳል። የእናት ውለታዋን መክፈል የሚችል ልጅ የለም። የእናት ፍቅርን ለመግለጽም በርካቶች አንደበታቸው ይተሳሰራል፤ ቃላት ይነጥፍባቸዋል፤ ስሜታቸውን መግራት ይሳናቸዋል። ድምፃዊ እሱባለው ይታየው(የሺ) ‘ይናገራል ፎቶ’ በሚል እናትና አባቱን በገለጸበት ሙዚቃ የመጨረሻው ማጠንጠኛው ‘እወድሻለሁ/እወድሃለሁ’ ያለው፤ እንዲሁም ድምፃዊት ብዙነሽ በቀለ ‘እናት ውለታዋ’ በተሰኘ ዘፈኗ ውስጥ (ዜማና ግጥም ጋዜጠኛ ሰለሞን ተሰማ)፤ “ወላጅ እናት እኮ ፍፁም በመንፈሷ፣ ልጇን ትወዳለች አብልጣ ከራሷ” እያለች በሚስረቀረቅ ድምጿ የምታንጎራጉረው ለዚህ ይመስላል። ዕውቁ የቋንቋ ሊቅ የሻው ተሰማ (የኮተቤው) ‘የጥቁር አፈር ትሩፋቶች’ በተሰኘው መጽሐፉ (ገጽ-79) ‘መቀነትሽን አጥብቂ’ በሚል ርዕስ ባሰፈረው ረዘም ያለ ግጥም ሁለት አንጓዎች ብቻ ስንመዝ የእናትነት ውለታን መመለስ እንደሚሳን፤ የእናትነት ግብሯ ‘እናት’ የሚለው ቃል በራሱ እንደሚያንስባት ያትታል። … “ለዚህ ወሮታሽ አጸፋ፤ እናት ይልሻል አገሩ፤ እኔም እናቴ ብልሽ መች ሊመጥንሽ ዳሩ። … እናትነት ምጡቅ ነው፤ እናት ከመባል ይልቃል፤ የግብርሽ ስንክሳር ዚቁ፤ በስያሜ መች ያልቃል”… በማለት ይገልጸዋል። መውጫ ዶክተር ይሁኔ የሴት እና እናትን የነገዋን መንገድ ከሳይንስ አተያይ አንጽረው፤ ከማኅበረ-ፖለቲካ፤ ከማኅበረ-ባህል ከፍታዋ አመሳክረው፤ እናትና ሀገርን መጋመድ አመስጥረው መልእክታቸውን እንደ መውጫ አስፍረዋል። ለስንበት አንድ አንቀጽ እንወርውር!! “የእናት ሀገር ህልውና ከእናቶች ሕይወት ጋር በቀጥተኛ ተዛምዶ አለው። የሰመረ ትውልድ ሊቀጠል የሚችለው በጥሩ ሁኔታ በተገነባ የእናቶች አቅም ነው። የእናቶች አቅም ሲገነባ የራሳቸውን አቅም ያውቃሉ፤ ምርጫቸውን በራሳቸው ይወስናሉ፤ እንዲሁም ለሚመጣው ማኅበራዊ ለውጥ የራሳቸውን አሻራ ያሳርፋሉ። ስለሆነም የእናቶችን አቅም ማጎልበት ትውልድን ማጎልበት ነው። እናቶች ላይ መሥራት ትውልድ ላይ መሥራት ነው”  
አድዋ የፓን አፍሪካዊነት እርሾ..
Mar 1, 2023 479
(አየለ ያረጋል) መንደርደሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የዛሬው አፍሪካ ሕብረት) ከተመሰረተ ዘንድሮ 60 ዓመታት ደፈነ። አፍሪካ ሕብረት በ2063 ለማሳካት ያቀዳቸው አህጉር አቀፍ ግቦች ትግበራ 10ኛ ዓመታት ሞልቶታል። 36ኛው የአፍሪካ ሕብረት መሪዎች ጉባዔ 'የአፍሪካ አኅጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ትግበራን ማፋጠን' በሚል መሪ ሃሳብ መካሄዱ በርካታ ፓን አፍሪካዊያን ዘንድ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበታል። ይሄውም የቀደምት አፍሪካዊያን ፖለቲካዊ ግቦች ወደ አፍሪካ አቀፍ ምጣኔ ሀብታዊ ሕልሞች ስኬት መንገድ ይመራል የሚል ብሩህ ተስፋ በማሳየቱ ነው። ቀደምት ፓን አፍሪካዊያን መሪዎች ሲሰባሰቡ አፍሪካን ከቅኝ ገዝዎች መንጋጋ ፈልቅቀው ነጻነቷ የተረጋገጠ፣ የዳበረችና ሕብረቷ የተጠበቀ አፍሪካን ዕውን ለማድረግ በመሻት ነበር። በዚህም ከአውሮፓዊያን ቅኝ ግዛት ቀድመው ነጻነታቸውን ያወጁ ሀገራት፤ ይህን ሕልማቸውን ዕውን ለማድረግ ድርጅት ሲጠነስሱ የሀሳብ ሜዳና መዳረሻቸው ኢትዮጵያ ነበረች። ለምን ቢሉ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻነት ዘፍጥረት ነጸብራቅ ናትና። ይሄ የሆነው ታዲያ በአድዋ እርሾ ላይ ተመስርቶ ነው። "አድዋ ድል የአፍሪካ ድል ነው። የኢትዮጵያ ትንሳኤ የአፍሪካ ትንሳኤ ነው" እንዲሉ የፓን አፍሪካዊነት አቀንቃኙ የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት። አፍሪካ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ መልከ ብዙ ፈተናዎች እየተናጠች ቀጥላለች። በየጊዜው ወደ አስከፊ ድህነትና ውስጣዊ መከፋፈል ቀውስ እያመራች ባለበት አሁናዊ መልኳ የአፍሪካ ሕብረት ህልሞች ይሳካሉ ወይ የሚለው የብዙሃኑ ስጋት ነው። እናም የፓን አፍሪካዊነት (Pan Africanism) እርሾ የሆነውን አድዋ ድልን ተጠቅሞ መነጋገር፤ የአፍሪካ እንጀራዋን መጋገርና ዕቅዷን መተግበር ሳያሻት አይቀርም። የአድዋ ድል የፓን አፍሪካዊነት እርሾነት (…) “አድዋ የደም ግብር ነው፤ አበው የለኮሱት ቀንዲልአድዋ የአፍሪካ ዱካ ነው፤ አበሽ የከተበው ፊደልላጥፋህ ቢሉት መች ይጠፋል፤ ጠላት በልቶ ያፈራ ተክልለዛሬም ታሪክ ነው፣ ‘ነገም ሌላ ቀን ነው’ ለሚል…”(ከደራሲና ጋዜጠኛ ነብይ መኮነን ‘ስውር ስፌት’ ከተሰኘው የግጥም መድብል የተቀነጨበ) የአድዋ ጦርነት ሰበብ የውጫሌ ውል ነው የሚለው ታሪካዊ ዕይታ ሰፊ ቦታ ይዟል። ዳሩ አሳማኙ የጦርነቱ መንስኤ ከውጫሌ ውል ይልቅ አፍሪካን በይፋ የመቀራመት ውሳኔ የተደረገበት በርሊን ጉባዔ ነው የሚል ምሁራዊ አተያይ አለ። ጉባዔው አፍሪካዊያንን ለዘመናት በባርነት ሲያግዙ የኖሩ አውሮፓዊያን አፍሪካዊያንን እንደ ሸቀጥ ከመጠቀም ባሻገር ሁለመና አንጡራ ሀብት ለመበዝበዝ የሜድትራኒያንን ባህር ተሻግረው አፍሪካን ለመቀራመት በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ያደረጉት ስምምነት ነበር። የኢትዮጵያ ዕጣም ለኢጣሊያ መንግስት ወጥቷል። አንዳንድ የታሪክ አተያዮች አጼ ዮሐንስ መተማ ላይ በተሰው በጥቂት ቀናት ልዩነት የተፈረመው የውጫሌ ውል ዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዙፋን ከተረከቡ በኋላ ራሳቸውን እስኪያደራጁ ለጊዜ መግዣ ያደረጉት ውል እንጂ ጦርነቱ አይቀሬነት ንጉሱ መጠርጠራቸው አልቀረም ይላሉ። ለዚህ ደግሞ የአድዋ ጦርነት የተደረገው የውጫሌ ውል ከተፈረመ ከአምስት ዓመታት በኋላ መሆኑ፤ በርግጥም አድዋ ጦርነት የበርሊን ጉባዔ ውሳኔ ጦስ እንጂ የውጫሌ ብቻ አይደለም የሚለው ሃሳብ ገዥነት ይኖረዋል። የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ታቦ ምቤኪ የአፍሪካ ቀን በተከበረበት በአንድ ወቅት "ከአድዋ ድል 11 ዓመታት ቀደም ብሎ በርሊን ላይ በተደረገው አፍሪካን የመቀራመት ጉባዔ፤ ከአድዋ ድል ማግስት ፉርሽ ሆነ። የበርሊን ጉባዔ ውሳኔ ወደ ግጭት እንዲያመሩ አደረጋቸው። አፍሪካ ቅኝ መገዛት አለባት የሚለውን እሳቤ ኢትዮጵያ በእምቢተኝነት ተቃወመች፤ በገቢርም አሳካቸው። ከተባበሩ ማንንም ሃይል ማሸነፍ እንደሚቻል ለአፍሪካዊያን ግልጽ መልዕክት አስተጋባች" በማለት አብራርተው ነበር። ቅድመ አድዋ የኢጣሊያን ጦር አዝማች ጄነራል ባራቴሪ ምኒልክን ጉሮሮውን አንቆ ወደ ኢጣሊያ ሀገር እንስሳት ማቆያ እንደሚያመጣው ለሀገሪቷ ምክር ቤትና በጠቅላይ ሚኒስትሩ ክሪስፒ ፊት ቃል ገብቶ ነበር። ከወራት በኋላ በተደረገው የአድዋ ጦርነት ግን ነገሩ የተገላቢጦሽ ነበር። የኢጣሊያ ወራሪ ጦር አድዋ ላይ የሽንፈት ካባ ተከናንቦ ተመለሰ። ጀኔራል ባራቴሪም ‘ጽድቁ ቀርቶ በቅጥ በኮነነኝ’ እንዲሉ በጦርነቱ ተዋርዶ የጀኔራል መኮነንነት ማዕረጉ ተገፎ የተጠያቂነት ፍርድ ተፈረደበት። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ኤምሬትስ ፕሮፌሰሩ ባህሩ ዘውዴ በአንድ ወቅት የአድዋ ክብረ በዓል ላይ ባቀረቡት ጽሁፍ “ጥቁር ሕዝቦች ከነጮች ጋር ያደረጓቸው ጦርነቶች ብዛት የትየሌለ ነው። አንድም ጦርነት ግን በነጮች ላይ ድል አልተጎናጸፈም፤ ከወርቃማው የአድዋ ድል በስተቀር” ማለታቸውን አስታውሳለሁ። በፕሮፌሰሩ አተያይ አድዋ አዲስ የታሪክ ምዕራፉ ሲከፍት በአንጻሩ ነባር አስተሳስብ ሰብሯል፤ የጥቁሮች የበታችነት ስሜትና የነጮች የበላይነት አስተሳስብ ለመጀመሪያ ጊዜ በአድዋ ተራሮች ግርጌ ተሽሯል። ፕሮፌሰሩ ‘ኢትዮጵያዊያን ለምን አሸነፉ’ የሚለው አመክንዮ ሲፈትቱም ቅድመ አድዋ ጦርነቶች ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያለልዩነት ህብረት መቆሙ፤ የአጼ ምኒልክ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንዲሁም በጦርነቱ ወቅት የነበረው የኢትዮጵያዊያን ታክቲካዊ የበላይነት እንደሆነ ይገልጻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በአንድ ወቅት “ታሪክን ለሚመረምር ትውልድ ዓድዋ ውስጥ ሕልውናን አፅንቶ የመኖር፣ ዓድዋ ውስጥ ዲፕሎማሲ፣ ዓድዋ ውስጥ ወታደራዊ ስትራቴጂ፣ ታላቅ ውስጣዊ የሕዝቦች ኅብረትና አንድነት፣ ጥበብና ተግባቦት፣ ፍቅርና መስጠት፣ ክብርና ጀግንነት ሞልቶና ሰፍቶ የነበረ መሆኑን እናያለን” ብለው ነበር።የአድዋ ድል ቱርፋቶች መልከ ብዙ፣ ቀለመ ደማቅ፣ አድማስ ዘለል ናቸው። አድዋ አገራዊ፣ አህጉራዊና ሉላዊ እሳቤን ለውጧል። በዚህ ጽሁፍ ግን የአድዋ ድል ቱርፋትን ከፓን አፍሪካዊነት አተያይ እንቃኛለን። አድዋ ድል ከኢትዮጵያዊያን ባለፈ ለለቀረው አፍሪካ፣ ሰፋ ሲልም ለመላው ጥቁር ሰብዓ ዘር ምን ፈየደ፤ ምንስ አተረፈ፣ ለኋላው ፓን አፍሪካዊነት ምን አበርክቶ ነበረው የሚሉ ተጠየቆች ሲፈተኙ ለዛሬዋና ለነገዋ አፍሪካ የሚበጁ ቁም ነገሮችን ነቅሶ ማውጣት ይቻላል። የአሜሪካው ሞርጋን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ተመራማሪው ዶክተር ጌታቸው መታፈሪያ የአድዋ ድል “አንድም ቅኝ ገዥዎች ኃያልነታቸው በአፍሪካዊያን እንደሚፈተን የተገነዘቡበት፤ ሁለትም የአፍሪካ ዳያስፖራዎች የተስፋ ስንቅ የታጠቁበት ነው። ባርነት፣ ጭቆና፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ብዝበዛዎች እልባት እንዲያገኙ ደወል አቃጭሏል። ልክ ዳግማዊ ምኒልክ ኢትዮጵያዊያንን ካለአንዳች ልዩነት አሰባስበው ጠላትን ድል እንደነሱት ሁሉ አርቆ አሳቢ አመራር ካለ አፍሪካዊያን እኩልነት፣ ፍትሕና የህልም እንጀራ የሆነባቸውን ሁለንተናዊ አህጉራዊ ሠላም ማግኘት እንደሚችል ወኔ ቆሰቆሰባቸው” ብለዋል። ዕውቁ የኢትዮጵያ ታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት “የአድዋ ድል ዜና በአውሮጳ ኃያላን ዘንድ የጦር አደጋ ጋረጠ፤ ሮምን በመሰሉ የአውሮጳ ከተሞች የፖለቲካዊ ቀውስ ምጽዓት ቀረበ፤ የእንግሊዛዊያንን ሸውራራ እሳቤም በአንድ ሌሊት ቀየረ” ይላሉ። እንደ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት ጥናት አድዋ ከትግል ባሻገር በደቡብ አፍሪካ፣ በላቲን አሜሪካ ‘ኢትዮጵያዊነት’ የሚል ሃይማኖት አስተምሮ እንቅስቃሴ ያስጀመረ ታሪካዊ ከስተትም ነው። በአድዋ ድል ማግስት ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በኢትዮጵያ ስም አያሌ አብያተ- ክርስቲያናት መታነጻቸውን ይዘረዝራሉ። ለአብነትም የተባበሩት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ ተልዕኮ በደቡብ አፍሪካ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ አፍሪካ፣ የቅዱስ ፍሊፕ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ አፍሪካ፣ የኢትዮጵያ የምህላ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ አፍሪካ እና የኢትዮጵያ ሰብዓ-ገነት የእግዚአብሄር መመስገኛ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የሚሉት ይገኙበታል። በተመሳሳይ የሚቺጋን ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ፕሮፌሰር ሃሮልድ ማርክስ “ለጥቁር ዳያስፖራዎች የኢትዮጵያ ድል ጮራ የወቅቱ ክብርና ለነጋቸው የይቻላል መንፈስ ያስታጠቃቸው ልዩ ክስተት ሆነም” ይላሉ። ምዕራባዊያኑ በጥቁሮች ላይ ለዘመናት ያሳደሩትን ጥላቻ፣ ዘረኝነት፣ ንቀት እንዲያጤኑ፤ ማድረጉን ይጠቅሳሉ። በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ተመራማሪው ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በበኩላቸው አድዋን ልዕለ አውራጃዊ ምልከታ፣ ልዕለ ዘውግ አስተሳስብ የታየበት የጋራ ነጻነት ዓርማ ሲያደርጉት፤ ዕውቁ የታሪክ ሰው ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦም አድዋን 'ኢምፔሪያሊዝምን ያሸነፈ ድል' በማለት ገልጸውታል። ‘የአድዋ ጦርነት’ በተሰኘው መፅሀፋቸው የሚታወቁት ፕሮፌሰሩ ሬሞንድ ጆናስ አንዳንድ የምዕራባዊያን አገራት የአድዋን ድል ለማንኳሰስ ቢሞክሩም ሙከራው ወንዝ እንዳላሻገራቸው ይጠቅሳሉ። ‘ታሪክ የተለየ ክስተትን ይወዳል’ የሚሉት ፕሮፌሰሩ አድዋ ተለምዷዊ ጉዞ የቀየሰ፣ ነባር ንግርን የለወጠ፣ ለአፍሪካዊያን ቅኝ ተገዥዎች የራስ መተማመን ጉልበት ያጎናጸፈ፣ በአጠቃላይ አድዋን የታሪክ ዑደትን የጨዋታ ሕግ የቀየረ ዕውነታ አድርገውታል። ፕሮፌሰሩ አክለውም ከአድዋ ድል ቱርፋት ሀተታቸው አድዋ አፍሪካን በዝባዥ ወራሪ ሃይልን ያስተማረ፣ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች በመላው ዓለም በበረቱበት በዛ ወቅት አጼ ምኒልክ ለምርኮኞቻቸው ያሳዩትን ርህራሄና ህዝቡን አስተባብሮ የመምራት ብልሀተቻው የታየበት ከዚህም ባሻገር ግን ለአፍሪካውያን ብሎም ለአፍሪካ አሜሪካውያን የፓን አፍሪካ እንቅስቃሴ ምልክት እና ለፓን አፍሪካን ራዕይ አቀንቃኞች ተምሳሌት ድል መሆኑን ጠቅሰዋል። የካናዳው ማክጊል ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና ምሁር ዶክተር ሜማይሬ ሜናሴማይ፤ አድዋ የማይቻል መሰል እውነት በገሃድ የታየበት ሁነት ነው፤ አዲስ ፖለቲካዊ ተጠየቅ የፈለቀበት፤ ታሪካዊ አድማስ የተከፈተበትም ዕለት እንደሆነ የሌሎች ምሁራንን ሃሳብ ይጋራሉ። በኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክ፣ ባሕልና አወቃቀር ጥናታቸው በስፋት የሚታወቁት ፕሮፌሰር ዶናልድ ሊቨን የአድዋ ዘመቻ ድል ፍሬ ለኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆን የሚሊዮን ጥቁሮች የኩራትና ወኔ ፏፏቴ ቅርስ እንደሆነ ይገልጻሉ። አድዋ ከአፍሪካዊያን ንቅናቄ መነሻነቱ ባሻገርም ለጥቁሮች መብት ታጋዩ ማርክስ ጋርቬይ “ኢትዮጵያ እውነተኛዋ የአባቶቻችን ምድር” በማለት ለ‘የምልሰተ አፍሪካ ንቅናቄ’ ቅስቀሳው ተጠቅሞበታል። እውቅ የጥቁር መብት ተሟጋቾች የሃይቲው ቤንቶ ሲልቫን፣ የምዕራብ ኢንዲያኖች ጆሴፍ ቪታሌን፣ እንዲሁም ቡከር ዋሽንግተን፣ ኢዳ ዌልስ፣ ዲ ቦይስ ‘የጺዮን ንጉስ’ ምልክት በማድረግ ለፀረ ቅኝ ግዛትና ዘረኝነት ትግል ቀስቅሰውበታል። በቅኝ ግዛት ቀንበር ስር ከነበሩ የአፍሪካና የላቲን አሜሪካ አገራት የነጻነት ታጋዮች መካከልም የናይጄሪያው ናምዲ አዝኪዌ፣ የጋናው ክዋሜ ንኩርማን፣ የኬንያው ጆሞ ኬንያታ፣ የጀማይካው ጆርጅ ፓድሞሬ በአድዋ ድል ዜጎቻቸውን በመቀስቀስና ከጎናቸው በማሳለፍ፣ ተከታዮችን አፍርተዋል። በአጠቃላይ ድሕረ አድዋ ድል ኢትዪጵያ ውስጥ ዘመናዊነት እንዲስፋፋ፣ የባቡር፣ ስልክ፣ ትምህርት፣ ፖስታ፣ ቴሌ፣ መንገድና ሌሎች መሰረተ ልማቶች እንዲዘረጉ፤ ኢትዮጵያ የትኛውም አፍሪካዊ አገር ያላገኘውን የራሷን የፖለቲካ ኢኮኖሚ እንድትመራ አስችሏታል። ታላቁ የአድዋ ድል ዘመናዊት ኢትዮጵያን ከጥንታዊ ታሪኳ ጋር ያዋደደ፤ የጥንቶቹን አባቶቻችን ጀግንነትና ለአገር ያላቸውን ፍቅር ያስመሰከረ፣ የነጻነት አይበገሬነት ወኔን ያሳዬ፣ የህዝቦች አንድነት ህያው ማሳያ ታሪካዊ ሁነት ነው። እናም አድዋ ለ’ፓን አፍሪካዊነት’ ጉዞ መሰረት ሆኗል፤ ቅኝ ግዛት እጣፈንታ አለመሆኑን አብስሯል። በርካታ የአፍሪካ አገራት ከቅኝ ግዛት ቀንበር ሲላቀቁ ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማትን ተሻምተዋል። አድዋ በሌሎች አገሮች ሕዝቦች የነጻነት ትግል ተምሳሌት ሆኖ በተለይም የጥቁር ዓለም ህዝቦችን ያነሳሳ፣ የኢትዮጵያዊነት መንፈስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲቀነቀን ያስቻለ ድል ነው።ኃያላኑ የምዕራብ አገራት ኤምባሲዎቻቸውን በአዲስ አበባ ከፍተው ለኢትዮጵያ ነጻና ሉዓላዊነት ‘አሜን’ ብለው ዕውቅና ሰጥተዋል። በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ ፖሊሲያቸውን ጭምር እንዲመረምሩ አድርጓል። አድዋ ከድሉ ማግስት ኢትዮጵያ ሉዓላዊት አገር መሆኗ እንዲረጋገጥ እና ድንበሯን እንድትካለልም አስችሏታል፡፡ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች እንድትታወቅ፣ ዝናዋ እንዲናኝና እንድትከበር ምክንያት ሆኗል፤ ለኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ማዕከልነት እርሾ ሆኗል። በዲፕሎማሲ ማዕከልነት ረገድ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ ትሆን ዘንድ አድዋ ወሳኙ እርሾ ነበር። ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር፣ ለተቀረው አፍሪካ የነጻነት ትግል ፋና ወጊ እንድትሆን በማድረጉ ትልቅ ሚና ነበረውና!! አፍሪካ ሕብረት እና ፓን አፍሪካዊነት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ1955 ዓ.ም በ32 ሃገራት አባልነት ተመሰረተ። በቅርቡ በአፍሪካ ሕብረት ቅጥር ግቢ የመታሰቢያ ሃውልት የቆመላቸው (በ32ኛው የሕብረቱ መሪዎች ጉባኤ ወቅት) ቀዳማዊ አፄ ሃይለስላሴና ካቢኒዎቻቸው ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት መመስረት ትልቅ ሚና ነው። ሕብረቱ ንጉሰ ነገስቱ ለአፍሪካ ነፃነትና አንድነት ላደረጉት ድጋፍና ለሕብረቱ መመስረት ለተጫወቱት ሚናን ታሳቢ በማድረግ መታሰቢያ ሐውልት አቁሞላቸዋል።የአፍሪካ ሕብረት የአህጉሪቷ ሁለንተናዊ ጉዳይ የበላይ ጠባቂ ነው። የፓን አፍሪካዊነት ውጤት የሆነው ይህ ተቋም ካሉት ተልዕኮዎች መካከል አህጉራዊ ሰላም፣ ፀጥታና ደህንነት ማረጋገጥ ዕድገትና ብልጽግናን ማበረታታት ነው። በእስካሁኑ እርምጃው ለአህጉሪቷና ሕዝቦቿ ሁለንተናዊ ደህንነትና ልማት አበርክቶቱ የሚተቸው ሕብረቱ በቅርብ ዓመታትም አፍሪካን ወደ በለጸገች አህጉር ለማሸጋገር የ2063 አጀንዳ ነድፎ ጉዞ መጀመሩ ይታወቃል። ይህን ሕልም ዕውን ለማድረግ “የሰላምና ደህንነት መዋቅሩን በበላይነት መምራት ይገባዋል” የሚሉ ወገኖች ግን ሕብረቱ ከአፍንጫው ሥር ያለውን ክፍለ አህጉራዊ ሰላምና ደህንነት መምራት ተስኖታል በማለት ይሞግታሉ። “ደጅ አስከባሪነቱን ተነጠቀ?” እንዴ ሲሉም ይጠይቃሉ።በአፍሪካ ጸጥታና ደህንነት ለማረጋገጥ መሪዎቹ በማህበረሰባቸው ውስጥ የፖለቲካን መነጣጠል ያጠበበ አካባቢ መፍጠር እንዳለባቸው ምሁራን ይመክራሉ። የምርጫ ኮሚሽኖችን በራስ ፍላጎት መቀየድ፣ በፓለቲካዊ ሐሳብ ልዩነቶች ሁሉን ማግለል ለአምባገነን መሪዎች መፈጠር ምክንያት ይሆናል። እናም በአህጉሪቷ የግጭት መንስኤ የሚያጠኑ ጠንካራ ተቋማት መገንባት አካታች ዴሞክራሲያዊ ምህዳር በመፍጠር አህጉራዊ ቁልፍ ጉዳዮችን ዕልባት ከተበጀላቸው የ2063 የአህጉራዊ መዋቅራዊ ሽግግር አጀንዳ ማሳካት ይቻላል። እናም የአፍሪካ መንግስታት ከህዝብ ጋር በተዋዋሉት ፖለቲካዊ ውል መሰረት በቅድሚያ መታደስ ያሻቸዋል። የወቅቱ ነባራዊ ሁናቴ የአፍሪካ ሕብረት ጸጥታና ደህንነቱን በበላይነት የመቆጣጠር ተስፋ ፓን አፍሪካን እንደ አካል ከመጠየቅ በላይ ይጠጥራል። የመሪዎች ጉባዔ እና ፓን አፍሪካዊነት የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ "የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን ማፋጠን" በሚል መሪ ሀሳብ የካቲት 11 እና 12 በአዲስ አበባ ተደርጓል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ አማካሪ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ስለዘንድሮው ጉባዔ በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ውስጣዊ ችግር ወጥታ ጉባዔውን በስኬት መስተናገዷ ብቻ ሳይሆን በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት የተፈታበት መንገድ ኢትዮጵያ አሁንም የአፍሪካን ችግር በአፍሪካ የመፍታት አርዓያነቷን ያሳዬ አጋጣሚ መሆኑን ጉባኤው በአድናቆት አውስቶታል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የፖለቲካ ጉዳዮች፣ ሰላም እና ፀጥታ ዘርፍ ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዲዎዬ በዘንድሮው መሪዎች ጉባዔ በኢትዮጵያ ለተደረሰው የሰላም ስምምነት ትልቅ አድናቆት የተቸረ እንደነበር ገልፀዋል። የኢትዮጵያ የሰላም ሂደት ተሞክሮ በ2063 የአፍሪካ የልማት አጀንዳ ውስጥ አንዱ በሆነው የተኩስ ድምፅ የማይሰማበት አፍሪካን ዕውን የማድረግ ግብ ማሳያ መሆኑንም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ተመራጭ የዲፕሎማሲ ማዕከል መሆኗን ያሳየችበት፣ በአንዳንድ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ይሰራጩ የነበሩ የተዛቡ ዘገባዎች ትክክለኛ መልክ የያዙበት እንደነበር በመግለጫው ተወስቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በመሪዎቹ ጉባኤ የመክፈቻ ንግግራቸው ከ60 ዓመታት በፊት የአፍሪካን ትብብር ለማረጋገጥ የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን የመሰረቱ ቀደምት አፍሪካውያንን ራዕይ አድንቀው የአፍሪካን መፃኢ ዕድል ብሩህ ለማድረግ ከቀደምት አባቶች አንድነት መማር እንደሚያሻ የቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴን ንግግር አውስተው ነበር። ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ የአህጉሪቱን ፈተናዎች በአፍሪካዊ ትብብር መቋቋምና መፍታት እንደሚቻል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ጠቅሰዋል። በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ መቀመጫ እንድታገኝ መጠየቃቸውና የዓለም አቀፉን ሚዲያ የተንሸዋረረ አተያይ ለመቀልበስ አፍሪካ አቀፍ ሚዲያ ማቋቋም እንደሚያስፈልጋት መጠቆማቸው ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካኒዝም ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንደሆነ አምባሳደር ታዬ ያነሳሉ። ይህ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጰያ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ መገንባቷ፣ ዘንድሮም ለመጀመሪያ ጊዜ የፓን አፍሪካ ጉባዔ ማዘጋጀቷ፣ የፓን አፍሪካ ወጣቶች ጉባዔ መመስረት እንዳለበት መጠየቋም ሌላው የፓን አፍሪካዊነት መሪነቷን አሁኑም ማስቀጠሏን ማሳያ እንደሆነ አምባሳደር ታዬ ጠቅሰውታል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የፖለቲካ ጉዳዮች፣ ሰላም እና ፀጥታ ዘርፍ ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዲዎዬ አፍሪካ የሰላምና ፀጥታን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በመንግስታቱ ድርጅት በኩል በቂና ተመጣጣኝ የፋይናንስ ድጋፍ እንደምትሻ፣ የሰላም ማስከበር ስምሪቶች ስኬታማነት ፋይናንስና በጀት ጉዳይ ትኩረት እንዲሰጠውና እንደ ፀጥታ ምክር ቤት አፍሪካም የራሷ አቅሙ የጎለበተ ተቋም መገንባት እንደሚጠበቅባት፣ መፈንቀለ መንግስትን ጨምሮ ኢ-ሕገ መንግስታዊ አካሄዶችን ህብረቱ አሁንም በፅኑ እንደሚያወግዝ ጠቁመው ነበር። በአፍሪካ ግጭት አፈታት ሂደቶች ጥበብና ብልሃት ያላቸውን አፍሪካዊ ወጣቶችን ጨምሮ ሁሉንም ህብረተሰብ ክፍል ማሳተፍ፣ አሳቢያንንና ምሁራንን ጥምረት በመፍጠር ተግባርና ንድፈ ሀሳብን በማጣጣም ውጤታማ ስራ ማከናወንና ዲፕሎማሲያዊ ስራን ማፋጠን እንደሚያም እንዲሁ። በተመሳሳይ ከኢኮኖሚ አንጻር የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የመሰረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሾነር ዶክተር አቡ ዘይድ አማኒ ደግሞ በሃይል፣ በትራንስፖርትና በዲጂታላይዜሽን ረገድ አፍሪካን እድገት ለማሳለጥ ስርዎችን አንስተዋል። ለአብነትም በአፍሪካ ሁለንተናዊ ዕድቷን ለማረጋገጥ አፍሪካ አቀፍ አንድ የኤሌክትሪክ ኃይል ገበያ እንዲኖርም ፍኖተ ካርታ መቀረፁን፣ ለአፍሪካዊያን ትስስር ለማሳለጥ በትራንስፖርት ዘርፍም በ35 ሀገራት የአንድ የአየር ትራንስፖርት ገበያ መፈጠሩን፤ በዲጂታላይዜሽን በኩልም በሁለም መስክ አፍሪካ አቀፍ የጋራ ገበያ እንዲፋጠን የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል። እነዚህ ተግባራትም ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራን ለማፋጠን የሚኖራቸውን ሁነኛ አስተዋጽኦ አብራርተዋል። በጉባዔው መዝጊያ ላይ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት እና ተመራጩ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር የኮሞሮሱ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሱማኒ በሰጡት መግለጫ፤ በ2023 አፍሪካ ሰላምና ፀጥታ ማረጋገጥ እና የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራን ቀዳሚ አጀንዳ አድርገው እንደሚሰሩ ገልጸው ነበር። አፍሪካ ያላት የተፈጥሮ ሀብት ማልማትና የንግድ ትስስሯን በማጠናከር ሁለንተናዊ ልማቷን ለማረጋገጥ፣ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናውን ትግበራን ማሳለጥ፣ የአፍሪካ ድምፅ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይሰማ ዘንድ በፀጥታው ምክር ቤት አባል እንድትሆን መጎትጎትን ጠቃቅሰዋል። አፍሪካ ዘላቂ ሰላምና ፀጥታ ለማረጋገጥ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እየሰጠ ያለው የገንዘብ ድጋፍ ኢ-ፍትሃዊነት መስተካከል እንዳለበትም የሰራ ኅላፊዎቹ በተደጋጋሚ አንስተዋል። አፍሪካ ለነገዋ የአድዋ ድልን ፓን አፍሪካዊነት እርሾ ብትጠቀምስ ኢትዮጵያ ለአፍሪካና ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ቀንዲልነቷ በታሪክ መዛግብት ሰፍሯል። ለአፍሪካና ለጥቁር ሕዝቦች ታሪክና ሥልጣኔ፣ ቅርስና ባህል፣ ነጻነትና መብት ያደረገችውን ተጋድሎ ጉምቱ ፓን አፍሪካዊያኑ ይስማሙበታል። ከደቡብ አፍሪካው የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ እስከ ኦሊቨር ታምቦና ታቦ ምቤኪ፣ ከዚሙባቡዌው ፕሬዚደንት ሮበርት ሙጋቤ እስከ ሴኔጋላዊው ሴዳር ሴንጎር፣ የኬኒያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታና ሌሎችም የአፍሪካ መሪዎች ኢትዮጵያ ‘‘የአፍሪካ እናት” ሲሉ ደጋግመው ገልጸዋታል። ኔልሰን ማንዴላ የነጻነት ረጅሙ ጉዞ (Long Walk to Freedom) በተሰኘ ግለ ታሪካቸው ‘‘ኢትዮጵያ በልቤ ውስጥ ሁልጊዜም ልዩ ቦታ አላት፤ የፈረንሳይን፣ እንግሊዝንና አሜሪካንን በጥምር ከምጎበኝ ወደ ኢትዮጵያ ሄጄ ኢትዮጵያን መጎብኘት የበለጠ ይስበኛል፣ ትልቅ ደስታንም ይሰጠኛል” ብለዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የታሪክና የሥልጣኔ መሠረት ናት ብለው ያምናሉ። የቀድሞ የኬንያ ፕሬዚዳንት እሁሩ ኬኒያታ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢህ አህመድ በዓለ ሲመት ወቅት ‘‘ኢትዮጵያ የአፍሪካ እናት’ ብለዋታል። የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ በአንድ ወቅት በአድዋ ድል ክብረ በዓል ላይ ተገኝተው "የአድዋ መሬት የተቀደሰ ነውና ጫማዬ ላወልቅ ግድ ይለኛል" ብለው ነበር። አድዋ የአፍሪካ ቅዱስ መሬት፣ ለቅኝ ግዛት አቀንቃኞች ሃፍረት ምንጭ እንደሆነ አስረድተው ነበር። መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ሚድራድ ከተማ ያደረገው የፓን አፍሪካኒዝም ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ፎርቹን ቻሩምቢራ ምክር ቤቱ የአፍሪካ ሕብረት የሚያወጣቸውን ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞቾ ትግበራ መከታተልና የአፈፃፀም ክፍተቶችን መጠቆም፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የዴሞክራሲ ባህል ማጎልበት፣ የአፍሪካዊያን ድምፅ የሚሰማባቸውን የጋራ መድረኮች ማመቻቸትና ሀሳብ የማንሸራሸር ዕድል በመፍጠር የተሰበሰቡ ምክረ ሀሳቦችን ለሕብረቱ አስፈፃሚ አካል የማቅረብ ተልዕኮ ይዞ እንደሚሰራ ይገልጻሉ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአውሮፓዊያኑ 1963 ሲቋቋም ዋናው ዓላማው ፖለቲካዊ ትብብር እንደነበር ገልፀው፣ አሁናዊ አፍሪካውያን ግን ከፖለቲካው ባለፈ በመካከላቸው ኢኮኖሚ ትስስር እንደሚያስፈልጋቸው ይጠቅሳሉ። ለዚህ ደግሞ ከቅኝ ገዥዎች አዕምሯዊ እስር ቤት ወጥተው በፖን አፍሪካዊነት እሳቤ መራመድ እንደሚገባቸው አንስተዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሀገራት ከቀድሞ ቅኝ ገዥዎቻቸው ጉያ ከመርመጥመጥ፣ ባህልና ኩራታቸው ከቅኝ ገዥዎቻቸው እሳቤ ከመቅዳት በበይነ አፍራካ አካሄድ፣ በፓን አፍሪካዊነት መርህ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ያነሳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በፓን አፍሪካ ፎረም ላይ ባደረጉት ንግግር የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በአፍሪካ ወጣት መሪዎችን ለማፍራትና ለፓን አፍሪካዊነት መጠናከር ዐይነተኛ ሚነ እንዳለው ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያም ለፓን አፍሪካዊነት ማንሰራራት የነበራትን ታሪካዊ የመሪነት ሚና አሁንም አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠው ነበር። ፎረሙ የፓን አፍሪካ መንፈስ እና የአፍሪካ አንድነትን እንደ አዲስ ትንሳዔው እንደሚያበስርም እንዲሁ። ሀገራት ከሰው ሰራሽ መልክዓ ምድራዊ የወሰን ሃሳብ መስመሮች፣ ከርዕዮተ ዓለም አጥሮች ወጥተው የተባበረች እና የበገለፀገች አፍሪካን ዕውን ለማድረግ አጀንዳ የሚቀርጽ፣ ተሻጋሪ ሃሳብ የሚያፈልቅ ችግር ፈች አፍሪካዊ ትውልድ መገንባት አስፈላጊ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ታቦ ምቤኪም የቀጣይ አፍሪካ መጻዒ ዕድልን በአድዋ ድል እርሾዎችን ተጠቅሞ መወሰን እንደሚያስፈልግ፣ የጥቁሮች አኩሪ ታሪኮችን ለትውልድ ማስተማር፣ ወጣቱን በፓን አፍሪካዊ ቅኝት መቅረጽ እንደሚያስፈልግ ይጎተጉታሉ። የአድዋ የኢትዮፐያ ትንሳዔ የአፍሪካ ትንሳኤ መሆኑን የገለጹትም ለዚህ ነው። “ኢትዮጵያዊያን እንዳደረጉት መላ ህብረተሰቡን ካንቀሳቀስን እናሸንፋለን። ግን ምን ያህሎቻችን የተማርን ሰዎች ስለ አድዋ እና ኢትዮጵያ ታሪክ እናውቃለን። በ2004 ሃይቲ 200ኛ 'ዓመቷን የነጻነት ቀኗን አክብራ ነበር። የሃይቲ ዜጎች ከአፍሪካ በባርነት የተወሰደዱ ሰዎች ናቸው። ሶስት ግዛተ አጼዎችን /ስርዓት መንግስታትን/ አሸንፈዋል። የብሪታኒያን፣ ስፔን እና በመጨረሻም ፈረንሳይን ሶስት ስርዓተ መግስታትን ያሸነፉ ጥቁሮች ታሪክ ነውና። ይህን ታሪክ መተረክ አለብን። በ18ኛው ክፍል ዘመን የሃይቱ፣ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የአድዋና በ20ኛው ክፍለ ዘመን የደቡበ አፍሪካ አፓርታይድ ትግል የተገኙ ድሎች ታሪክ መንገር አለብን። እርስ በርስ የተሳሰሩ የአፍሪካዊያን የነጻነት ታሪኮች ናቸው። ትልቁ እንደ አህጉር ያለብን ከፍተት እኛ አፍሪካዊያን ወጣቶች ስለራሳቸው እንዲያውቁ እና እንዲነሳሱ ማስቻል ላይ ነው። ስለራሳቸው እንድንኮራና ስለማንነታቸው ያላቸው ስሜት በማነሳሳት አፍሪካዊያን ወጣቶች አህገሪቱ ሁለንተናዊ ሽግግር እንድታመጣ ማስቻል ይገባል። አድዋ ተጠቂዎች ሳይሆን አሸናፊዎች እንደምንሆን አሳይቶናል። አድዋን መዘከር የሚያስፈልገውም ለዚህ ነው" ነበር ያሉት።
ትንታኔዎች
የአየር ንብረት ፋይናንስ-አፍሪካውያን ገፍተው ያልሄዱበት መንገድ
Feb 18, 2023 477
/በገዛኸኝ ደገፉ/ የአፍሪካ ቀንድ ከ40 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ አያቅም የተባለለትን የድርቅ አደጋ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ሆነዋል። የድርቁ አደጋ የከፋበት የአፍሪካ ቀንድ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ተሸክመዋል። በተጨማሪም የከተሞች መስፋፋትና የከተሜነት የኑሮ ዘይቤን እያስተናገደች ባለችው አፍሪካ የኃይል እጥረት፣ በቂ የመሰረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ አለመኖር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት፣ ሥራ አጥነት ብሎም የወንጀሎች መስፋፋት አሕጉሪቱን ክፉኛ እየፈተኗት ይገኛሉ። የገጠር መሬት ምርታማነት መቀነስ ከገጠር ወደ ከተማ ለሚደረገው ፍልሰት አንደኛው ገፊ ምክንያት ሲሆን ለመሬቱ ምርታማነት መቀነስ ሰበብ ተደርጎ በዋናነት የሚጠቀሰው ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት የሚወልዳቸው የውኃ ኃብት መቀነስና ለተከታታይ ዓመታት የሚዘልቁት የድርቅ አደጋዎች መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አወሳስቦታል። እንደ አህጉር ከ4 በመቶ ያነሰ የካርቦን ልቀት ያላት አፍሪካ 65 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ መሆን ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚህ ችግር ሙሉ ለሙሉ መውጣት ባይቻልም ትርጉም ባለው ደረጃ መቀነስ እንዲቻል አህጉሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ኃብትና ወጣት የሰው ኃይል በማስተሳሰር ለውጥ ማምጣት ግድ ይላታል። በአፍሪካ የማይቀረውን የከተሞች መስፋፋትም ሆነ የህዝቦቿን የመልማትና የመለውጥ ፍላጎት ማሟላት ካለባት የአየር ንብረት ፋይናንስን የበለፀጉ ሀገራት ገቢራዊ ሊያደርጉት ይገባል። የአየር ንብረት ፋይናንስ (Climate Finance) የአካባቢ፣ ብሔራዊ ወይም ድንበር ተሻጋሪ ፋይናንስን የሚመለከት ሲሆን ከሕዝብ፣ ከግል እና ከአማራጭ የገንዘብ ምንጮች የተውጣጣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ስምምነት ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል እና የፓሪስ ስምምነት ደግሞ ሰፊ የገንዘብ አቅም ካላቸው አገራት አነስተኛ የኃብት አቅም ላላቸው እና ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ አገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት ነው። ስምምነቱ “የጋራ ግን ደግሞ ልዩነት ያለው ኃላፊነትና አቅም” በሚለው መርህ መሰረት ያደጉ አገሮች አዳጊ አገራትን ለመርዳት የገንዘብ ምንጮችን እንዲያቀርቡ ይጠይቃል። ፋይናንሱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ወሳኝ ድጋፍ እንደሚሆን ታምኖበታል። ምክንያቱም ልቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ላቅ ያለ የኢንቨስትመንት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ። በተመሳሳይ ከአሉታዊ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎች ጋር ለመላመድ እና ተለዋዋጭ ጫናዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። ከጥቂት አሥርት ዓመታት በፊት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የምእተ ዓመቱ የልማት ግብ ሰነድም ሆነ በቅርቡ በሚጠናቀቀው ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት ቢሰጠውም እስካሁን ግን የፈየደው ነገር የለም። አፍሪካ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችን ለመላመድ ዓመታዊ 41 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ክፍተት ይገጥማታል። ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ እያስተናገደች ባለችው 36ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ የአየር ንብረት ፋይናንስ ገቢራዊ ማድረግን ቀዳሚ ትኩረታቸው መሆን እንዳለበት የአንድ ዘመቻ (ONE Campaign) አጽንኦት ሰጥቶ ምክረ ሃሳቡን ሰንዝሯል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የአንድ ዘመቻ ዳይሬክተር ዶሪን ኒኒናሃዝዌ የአፍሪካ መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመላመድ ፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን አስከፊ ተጽዕኖ የመቋቋም አቅም እንዲገነቡ መክረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝቦቿ ለከፋ ጥቃት እየተዳረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች የበለጸጉ አገሮች የገቡትን የማላመድ ፋይናንስ ድጋፍ ቃል እንዲፈጽሙ ከማግባባት ባለፈ ማሳሰብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ ማለት እኤአ ከ2020 እስከ 2025 በዓመት 100 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመተውን ግብ የማሳካት ተግባር የሚጠይቅ ነው። ከዚህ ባሻገር በቀጣዮቹ ዓመታት በተጨመሩ መዋጮዎች የሚስተዋሉ ጉድለቶችን መፍታት እና በግብጿ ሻርም ኤል ሼክ ከተማ ባስተናገደችው COP-27 ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ለመላመድ በእጥፍ ፋይናንስን የማቅረብ ቁርጠኝነት የማቅረቢያ ዕቅድ ሊነድፉ ይገባል ነው ያሉት። የአፍሪካ አገሮች ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ጋር ሲታገሉ ቢቆዩም አሁን ላይ “አፍሪካ በአፈፃጸሙ ላይ መጠነኛ መሻሻል አሳይታለች” ብለዋል። እናም በ36ኛው የመሪዎቹ ጉባዔ የተገኙ ስኬቶች እና የጠፉ ዕድሎች እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማዎች ለማሳካት በአየር ንብረት ፋይናንስ በጥልቀት መክረው ለተሻለ ስኬት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዋና ዳይሬክተር አንቶኒዮ ቪቶሪኖ በአየር ንብረት ምክንያት የሚፈጠሩ መፈናቀልን ለመግታት የተሻሻሉ የመላመድ እና የተጽዕኖ ቅነሳ ተነሳሽነት ገቢራዊ ለማድረግ በአገራት መካከል ጠንካራ አጋርነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያሰምሩበታል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ኑሯቸውን መሰረት ባደረጉ ህዝቦች ላይ አውደ-ተኮር መላመድ እና የመቋቋም አቅም ግንባታ መፍጠር ይገባል። ለዚህ ደግሞ መላመድን የሚደግፉ ፋይናንስ ለማግኘት የሚረዱ መመሪያዎች ይበልጥ የተፍታቱ መሆን ይኖርባቸዋል ሲሉ ቪቶሪኖ ይሞግታሉ። ከ 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተጓዳኝ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ (High-Level Forum) ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በሻርም ኤል ሼክ በተካሄደው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መላመድን፣ መከላከልን እና ዝግጁነትን ለማሻሻል ዓለም አቀፍ ትብብር ማጎልበት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አውስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ ያወጣቸው የስምምነት ማዕቀፎች (United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC)) በርካታ ዝርዝርና ሚዛናዊ አካሄዶችን የያዙ ናቸው። ያም ሆኖ አተገባበራቸው እዚህ ግባ የማይባል በመሆኑ የሚታሰበውን ያህል ለውጥ ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። በዚህም ቦረና ዞንን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የአየር ንብረት መዛባት፣ የሙቀትና የባህር ጠለል መጨመር፣ ጎርፍ፣ ድርቅ እንዲሁም ያልተገመቱ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። ዳሩ ግን አገራትን፣ አህጉርን፣ ዓለምን እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ግዙፍ ኩባንያዎችን ያስተሳስራል የተባለለት የአየር ንብረት ፋይናንስ በቅጡ ገቢራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች ዳፋውን ለመጋፈጥ ተገደዋል። የአየር ንብረት ፋይናንስን በመተግበር በመስኩ የተጎጂዎችን ቁጥር ሊቀንሱና የዓለምን ሥነ-ምህዳር ከተቻለ ወደ ቀድሞው ሊመልሱ አሊያም አሁን ባለበት አረጋግተው ሊያቆዩ የሚያስችሉ በርካታ አማራጮች ተግባራዊ ሊደረጉ ይገባል። ለአብነትም ለድሃ ሃገራት አርሶ አደሮች የግብርና ምርቶች ተገቢውን ዋጋ በመክፈል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን እንዲቋቋሙ ማድረግ ከአማራጮቹ መካከል አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግዙፎቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሚያስወግዷቸው በካይ ጋዞች ተመጣጣኝ የጤና ሥርዓት በመዘርጋት የታዳጊ ሃገራት ዜጎችን የጤና አገልግሎት ማሻሻል ሌላው አማራጭ ነው። የተፈጥሮ ኃብቶችን የሚጎዱ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተፈጥሮን በሚንከባከቡ ዘዴዎች መተካት እንዲሁም ብክለትን የሚያስቀሩ የምርት ሂደቶች መለማመድ ጥቂቶቹ የመፍትሄ አማራጮች ተደረገው የሚወሰዱ ናቸው። በፓሪስ ከተደረሰውን የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ 1994 ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም (Global Environment Facility-GEF) COP-16 ዓለም አቀፍ ጉባዔ በኋላ በ2010 አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund-GCF) እንዲሁም በ2001 ደግሞ ልዩ የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (Special Climate Change Fund-SCCF) እና የመላመድ ፈንድ (Adaptation Fund-AF) የተባሉ ማዕቀፎች የተዘጋጁ ቢሆንም ስለጉዳዩ የሚያስረዱ ተከታታይ ስብሰባዎች ከማዘጋጀት በዘለለ ብዙ ርቀት መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። በቅርቡ በአለም ባንክ አሰባሳቢነት በኬንያ ናይሮቢ ተዘጋጅቶ በነበረው የአህጉሪቱን መሪዎች ባለሃብቶችንና ምሁራንን ባካተተውና “One Planet Summit” በተሰኘ መሰል ጉባዔ ላይም አፍሪካውያን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚገጥማቸውን ችግሮች ተከላክለው ሁለንተናዊ ዕድገታቸውን እንዲያፋጥኑ ካስፈለገ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምጣኔ ኃብት ፖሊሲ አዘጋጅተው መተግበር እንደሚኖርባቸው መግባባት ላይ የተደረሰ ቢሆንም አሁንም ጥያቄ ያስነሳው አፈጻጸሙ ስለመሆኑ ብዙ ተብሎለታል። ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ የተባለ ድርጅት ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው አፍሪካ እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር ከ 2020 እስከ 2030 ባሉት አሥር ዓመታት 2 ነጥብ 8 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር አሊያም በየዓመቱ ከ2 መቶ ሃምሳ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን አህጉሪቱ ከዘርፉ እያገኘችው ያለው ገንዘብም ከሚያስፈልጋት 12 በመቶውን ወይም 30 ቢሊየን ዶላር ብቻ ስለመሆኑ አስነብቧል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ሊሰሩ የሚችሉ በርካታ ተግባራት እንዳሏት የሚያትተው ሪፖርቱ ከአየር ንብረት ፋይናንስ የሚገኘው ገንዘብ በትራንስፖርት፣ በኃይል ልማት፣ በኢንዱስትሪ ብሎም በግብርና፣ በአፈርና በደን ኃብት አጠቃቀም ውጤታማ በሆነ መንገድ ከዋለ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ኃብቶች መንከባከብ ከማስቻሉም ባለፈ ላቅ ያለ ፋይዳ ይኖራዋል ብሏል። ይህ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖው ያስረዳል። ላለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ገቢራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራን የማስፋፋትና የተጎዱ አካባቢዎችን የማከም ሥራ እንዲሁም አይቀሬ የሆኑትን ከተሜነትና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ታሳቢ ያደረጉ የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ለአፍሪካ ሃገራት እየፈጠረው ያለው በጎ ተጽዕኖ በግልጽ እየታየ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ጥረት ግን በአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲደገፍ አገራዊና የተቀናጀ አሕጉራዊ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል። ከአጠቃላይ የአፍሪካ አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ግብጽ ብቻ 151 ቢሊየን ዶላር ከአየር ንብረት ንብረት ፋይናንስ ማግኘት እንደሚኖርባቸው የክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ ሪፖርቱ ይገልጻል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በመጭው የCOP-28 ጉባዔ የራሷንና የአፍሪካን ፍላጎት የሚያስጠብቁ የፋይናንስ ትልሞችን የመንደፍ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ የ COP-27 ጉባዔ ለአፍሪካ ያስገኘውን ውጤት እና አንድምታ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የመሪዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አስተባባሪ በሆኑት በኬንያው ፕሬዝዳንት ሰብሳቢነት በኅብረቱ የአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ በጥልቀት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ጥረቷን የሚያጎለብት የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ጠንካራ ተሳትፎ ልታደርግ ይገባል። የአፍሪካ አገራት ገፍተው ረጅም ርቀት ያልሄዱበት የአየር ንብረት ፋይናንስ እና ሌሎች የድጋፍ አማራጮችን በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት በመጠቀም የአየር ንብረት ተጽዕኖን የሚቋቋሙበት ጠንካራ አቅም ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል። በእርግጥም አፍሪካውያን መሪዎች በሚያደርጉዋቸው ስብሰባዎች በየማዕዝናቱ በድርቅ ሳቢያ ለምግብ እጦት የተዳረጉ ህዝቦቻቸውን የሚታደጉበት ሁነኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበትን ዘዴ ነድፈው ረጅም ርቀት ሊጓዙ ይገባል። ”
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 449
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ - የአፍሪካ የዘመናት ፈተና
Feb 13, 2023 446
በረከት ሲሳይ በርካታ የአፍሪካ አገራት ነፃነታቸውን ከተቀዳጁበት ከ1960ዎቹ ጀምሮ እስካሁን እልባት ካልተገኘላቸው አፍሪካዊ ጉዳዮች መካከል ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ አንዱ ነው። ለዚሁ ጉዳይ በርካታ መነሾ ቢኖሩትም ቅኝ ግዛቱ የፈጠራቸው ፖለቲካዊ ስንጥቃቶች፣ ድህነትና ሌሎች ማኅበራዊ ምስቅልቅሎሽ ለእነዚህ የጸጥታ ችግሮች በአብዛኛው የሚነሱ ምክንያቶች ናቸው። በአህጉሪቱ ላለፉት 40 እና 50 ዓመታት መቋጫ በሌለው መልኩ እዚህም እዚያም የሚነሱ ግጭቶችና ጦርነቶች ለአያሌዎች ሞትና የአካል ጉዳተኝነት ለገሚሱ ደግሞ ለዘመናት ከኖረበት ቀዬ እንዲሰደድ ምክንያት ሆነዋል። በብዙ ጥረት የተገነቡ መሰረተ-ልማቶች ወደ ፍርስራሽነት እንዲለወጡና በሂደት ላይ ያሉ የዘመናዊ አገር ግንባታ ሂደቶች እንዲስተጓጎሉና በፈተናዎች እንዲታጀቡ አድርጓል። ይህንኑ ኢኮኖሚያዊ ኪሣራ በሚያሳይ መልኩ፤ የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ከሁለት ዓመታት በፊት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያሳየው፤ በአፍሪካ የሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች በየዓመቱ የአገራቱን አጠቃላይ አገራዊ ምርት (ጂ ዲ ፒ) እድገት ከ4 በመቶ እስከ 6 በመቶ እንዲቀንስ ያደርገዋል ይላል። በተለይም ደግሞ በኢኮኖሚው ላይ የሚከሰቱ ችግሮች ተጽዕኖ ዓመታትን የሚዘልቅ በመሆኑ ተደራራቢና ድግግሞሽ ያሏቸው ችግሮች እንዲበራከቱ በር ከፍቷል። በእነዚህ ድርብርብ ውጥንቅጦች በአህጉሪቱ በከባድ ድህነት የሚኖሩ ዜጎች ህይወት ይበልጡኑ እንዲወሳሰብባቸውና ለከፋ ማኅበራዊ ችግር እንዲጋለጡ እያደረገ ነው። ከዚህም ባለፈ የጸጥታ ችግሮች በአፍሪካ ሳያባሩ መቀጠላቸው ዛሬም ጉዳዩን በአንክሮ እንድንመለከተው ያስገድደናል። ይህንን በሚያስረግጥ መልኩ ያለፈው የፈረንጆች ዓመት (2022) ግጭቶች የተስተዋሉበት ዓመትና በዘንድሮ ዓመት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩ ተመላክቷል። በሰላም ስምምነት የተቋጨውን በኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረውን ጦርነት ጨምሮ እስካሁን እልባት ያልተገኘላቸው የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና የደቡብ ሱዳን የጸጥታ ችግሮች ተጠቃሽ መሆናቸውን ነው የአፍሪካ የደኅንነት ተቋም ሪፖርት የሚያሳየው። ከዚህ ጎን ለጎን በሳሀል፣ በቻድ ሃይቅ ሸለቆ፣ በምስራቅ አፍሪካና በሰሜን ሞዛምቢክ ጸጥታን የሚያውክ የጽንፈኝነት እንቅስቃሴ መኖሩንም አመላክቷል። ከዚህ ጎን ለጎን በቡርኪና ፋሶ፣ በጊኒ፣ ማሊ፣ ሱዳን፣ ቻድ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ጅቡቲ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ማዳጋስካርና ኒጀር የተሳካና ያልተሳካ የመፈንቅለ-መንግሥት (ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ) ሙከራ መካሄዱንና የፖለቲካ አለመረጋጋት እንደተስተዋለባቸው ነው ሪፖርቱ ያወሳው። መንግሥታዊ የአስተዳደር ግድፈቶች፣ ምርጫን ተከትሎ የሚቀሰቀስ አለመግባባትና ሌሎችም በአህጉሪቱ ላለፉት ሁለት ዓመታት የተከሰቱ የጸጥታና የደኅንነት ችግሮች ለተያዘው የፈረንጆች ዓመትም ትልቅ ሥጋት መሆኑን ነው ያነሳው። አፍሪካ ኅብረት በበርካታ አገሮች የጸጥታ ችግሮች እንዲቆሙና እንዲረጋጉ በማድረግ አዎንታዊ ሚና መጫወቱ ተገልጿል። ለአብነትም በኢትዮጵያ በዘላቂነት ግጭትን ለማቆም የተደረሰው የሰላም ስምምነት ተጠቃሽ ሲሆን በሌሎችም አገራት ወደ ተሻለ ፖለቲካዊ መረጋጋት እንዲመጡ ትልቅ ሥራ ሰርቷል። ይህም ሆኖ አሁንም ድረስ ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ በኩል በርካታ ሥራ እንደሚቀር ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ በምዕራብ ሳሀል ያለው ከአልቃይዳና ከአይ ኤስ ጋር ግንኙነት ያለው ጽንፈኛ ቡድን በአካባቢው የፈጠረው አለመረጋጋት፣ ከማሊ የፈረንሳይ ጦር መውጣትና ማሊ ራሷ ከሳሀል ቡድን አምስት የጸጥታ መዋቅር መውጣቷም ሌላው የአህጉሪቷና የአካባቢው ራስ ምታት ሆኗል። የቻድ ሃይቅ ሸለቆ አካባቢ (በኒጀር፣ ቻድ፣ በካሜሮንና ናይጄሪያ) የሚስተዋለው የቦኮሃራምና ሌሎች የጽንፈኝነት እንቅስቃሴ፣ በምስራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ራሱን ኤም23 በማለት የሚጠራው ቡድን ከማዕከላዊ መንግሥት ጋር ጦር መማዘዙ እንዲሁም በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው በመንግሥትና በተቃዋሚ መካከል የተቀሰቀሰው የሽምቅ ውጊያ አሁንም አለመቆሙ፤ የአፍሪካ ኅብረት ጸጥታን በተመለከተ በዚህ ዓመት ትኩረት ሊያደርግበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ነው የእንግሊዙ ቻም ሃውስ የተሰኘው የጥናት ተቋም መረጃ የሚያመለክተው። በተያዘው የፈረንጆች ዓመት በተለያዩ ደረጃ የሚካሄዱ 17 ብሔራዊ ምርጫ መኖራቸውንና ይህንንም ተከትሎ ሊከሰቱ የሚችሉ የድኅረ-ምርጫ ፖለቲካዊ ግጭቶችን በማስቀረት ረገድ አፍሪካ ኅብረት አዎንታዊ ሚና መጫወት እንደሚጠበቅበትም ተመላክቷል። የአፍሪካ ኅብረት ቀጣይ አቅጣጫስ? አፍሪካ ኅብረት በበርካቶች አይን ሲታይ ምንም እንኳን የፖሊሲና የስትራቴጂ ችግር ባይኖርበትም ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ በበርካታ ጉዳዮች ላይ ችግሮች ተስተውሎበታል። ለዚህም ተቋሙ ካለበት የፋይናንስና ሌሎች ተያያዥ የቴክኒክ ችግሮች በተጓዳኝ በዋነኛነት አባል አገራት በኅብረቱ ቻርተር በመመራት ረገድ በርካታ ክፍተቶች መኖራቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በተለይም በጸጥታና ደኅንነት ምክር ቤት በኩል የሚወስናቸው ስምምነቶች ገቢራዊ አለመሆናቸው ትልቅ ክፍተት ሲሆን ምክር ቤቱም በቅርቡ ያደረገው ስብሰባ ይህንኑ አጋልጧል። ይህም አፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ መልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ እንዲጎለብት በማድረግ ረገድ ያለው ቁርጠኝነት ልዩ ትኩረት የሚሻ መሆኑን አመላክቷል። ለአብነትም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2020 የጥይት ድምፅ የማይሰማባት አህጉር ለመፍጠር ያቀደው ዕቅድ ምንም እንኳን ዕቅዱ ከጅምሩም ቢሆን ያለው ነባራዊ ሁኔታና የግጭቶች የመስፋፋት አዝማሚያ ከግምት በማስገባት ሊሳካ እንደማይችል በርካታ የመስኩ ተንታኞች ቢናገሩም ኅብረቱ በዚህ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት አልቻለም። ለዚህም ደግሞ በቀዳሚነት ምንም እንኳን የአባል አገራት የፖለቲካ ቁርጠኝነት ማነስ ትልቁን ድርሻ ቢይዝም የሚወስዳቸው እርምጃዎች ሳይሸራረፉ ተግባራዊ ለማድረግ መቸገሩን ነው የሚያሳዩት። በአፍሪካ በሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ሥራዎች በቁርጠኝነት መሥራት ይገባል። በተለይም ደግሞ አፍሪካ ኅብረት በቅርቡ ዳግም የከለሰውን በአህጉሪቱ የጥይት ድምፅ ለማጥፋት የወጣውን ፍኖተ- ካርታና እንዲሁም የክትትልና የግምገማ ማዕቀፍ ፈጥኖ ወደ ሥራ ማስገባት ይኖርበታል። ይህንንም ተከትሎ በጸጥታና የደኅንነት ምክር ቤቱ ያቋቋመውን የባለሙያዎች ቡድን የያዘ ማዕቀብ ለመጣል የሚሰራው ንዑስ ኮሚቴም በአግባቡ መጠቀም አለበት። አሁን ላይ በአህጉሪቱ ለጸጥታ መስፈን ሥጋት በሚሆኑና በሚያቆጠቁጡ ጉዳዮች ላይ እልባት ለመስጠት መረባረብ እንዳለበት ነው የሚጠቀሰው። በተመሳሳይ የሚወስዳቸው እርምጃዎችም በባህሪያቸው ተከታታይነትና ወጥነት ያላቸው እንዲሁም ችግሮች ከተፈጠሩ በኋላ ሳይሆን ከመፈጠራቸው በፊት አስቀድሞ መከላከልና ማክሸፍ ላይ ሊረባረብ እንደሚገባ ነው የሚያነሱት። ከዚህ በተጓዳኝ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማፋጠን የሚያስችሉ የአገራትን የፖለቲካ እንቅስቃሴ መደገፍና በዘላቂነት ዴሞክራሲ ባህል እንዲሆን የሚያስችሉ ሥራዎችን መደገፍ እንዳለበትም ነው የሚነሳው። በተለይም ደግሞ ወጣቶችን ያሳተፉ የዴሞክራሲ ግንባታ ሥራዎች በስፋት መሠራት እንዳለበት ነው የሚጠቀሱት። ከዚህ ጎን ለጎንም የአፍሪካ የእርስ በርስ መገማገሚያ መድረክም (ፒር ሪቪው ሜካኒዝም) በተለይም መልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲጎለብት በማድረግ ረገድም አበርክቶው ከፍ እንዲል መሠራት ይጠይቃል። የሰላም ሥራውን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችለውን የሰላም ፈንድም ማሰባሰብ እንዳለበትም ነው የሚነሳው። ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት አጋማሽ ላይ የሰላም ፈንዱ አጠቃላይ ገቢ 328 ሚሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 22 አባል አገራት ሙሉ በሙሉ እንዲሁም አምስት አገራት ደግሞ በከፊል የሚጠበቅባቸውን መዋጮ አዋጥተዋል። በሌላ በኩል 28 አባል አገራት ደግሞ መዋጮውን መክፈል አለመቻላቸውን ነው የአፍሪካ ኅብረት የሰላምና ደኅንነት ሪፖርት የሚያመለክተው። በመሆኑም አፍሪካ ኅብረት አባል አገራት የሚያዋጡትን ገንዘብ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጨርሱ ቅስቀሳ ማድረግን በአፍሪካ ጥላ ሥር በተለያዩ አገራት የሚያንቀሳቅሰውን የሰላም ሥራ ውጤታማ ማድረግ ይገባዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(ተ.መ.ድ) የጸጥታ ምክር ቤት ጉዳይ ላለፉት 15 ዓመታት በአፍሪካ መሪዎች በስፋት የተቀነቀነው አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት ይገባል የሚለው ጉዳይም አፍሪካ ኅብረት በዘንድሮ ጉባዔው ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። ምክር ቤቱ ከሚመለከታቸው ጉዳዮች ውስጥ ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑት አፍሪካን የተመለከቱ መሆናቸውና ይህም ሆኖ በምክር ቤቱ ውስጥ አፍሪካ አለመወከሏ የፍትሃዊነት ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል። በርካታ የአፍሪካ መሪዎች እንዲሁም ኅብረቱን በሊቀ-መንበርነት የመሩት እስከ ወቅቱ ሊቀ-መንበር የሴኔጋሉ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል ድረስ ጥሪያቸውን በተለያዩ መድረኮች አሰምተዋል። አሁን አሁን ላይም ጥያቄውን ምንም እንኳን የሩቅ ምስራቆቹ ጃፓንና ቻይና እንዲሁም ሕንድ አስቀድመው ቢቀበሉትም በተለይም አንዳንድ የምዕራብ አገራት ያሏቸውን የሃሳብ እቀባ በማንሳት ጉዳዩን እንዲጋሩት በማድረግ አፍሪካ ትልቅ ስኬት አግኝታለች። ይህም ሆኖ አሁንም አፍሪካ ስንት መቀመጫ ይኑራት? እንዲሁም ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ይሰጣት ወይስ አይሰጣት? የሚለው ጉዳይ ላይ ክርክሮቹ እንደቀጠሉ ነው። በዘንድሮ ጉባዔው ኅብረቱ በእነዚህ ጉዳይ ላይ ተወያይቶ ወደ መጨረሻ ምዕራፍ ላይ የሚደረስበትን ውሳኔ ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል። ይህንንም ማድረግ ከተቻለ በአፍሪካ ቀደምት መሪዎች ሲቀነቀን የቆየውን "አፍሪካዊ መፍትሔ ለአፍሪካ ችግሮች" የሚለውን ብሂል እውን ለማድረግና አህጉሪቷ ላይ ዘላቂ ሰላምና ደኅንነትን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ላይ አዎንታዊ አበርክቶ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
ጠንካራ አንድነት - ለዘላቂ ሰላም መሰረት!
Feb 3, 2023 400
በእንግዳው ከፍያለው (ባህር ዳር ኢዜአ) በረጅም እንጨት ጫፍና ጫፍ በገመድ ታስረው የተንጠለጠሉ ቋጠሮዎችን ተሸክማ ከጓደኞቿ ጋር ገበያ እየሄደች ነበር የተገናኘነው። ወጣት ማሪማ ሜካ ትባላለች፤ ዕድሜዋ ከሃያ ዓመት አያልፍም። በእንጨቱ አንደኛው ጫፍ 10 ሊትር አረቄ የያዘ ጀሪካን፤ በሌላኛው ጫፍ ደግሞ ሌላ ቋጠሮ በማንጠልጠል ተሸክማለች። ሸክሙን በትካሸዋ ላይ ጣል እድርጋ ፈጠን እያለች ስትራመድ ላየ በፊቷ ላይ አንዳች የብርታትና የጽናት መንፈስን ያነባል። እንደእኔ ለአካባቢው እንግዳ የሆነ ሰው “ሴት ልጅ እንዴት ይህን ያህል ክብደት ተሸክማ ትጓዛለች?” ብሎ ራሱን ሊጠይቅ ይችላል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማንዱራ ወረዳ ነዋሪዋ ወጣት ማሪማ ግን ሸክሙ እንደ ኩበት ቀሏት ይሁን ጽናቱን ፈጣሪ ሰጥቷት ባላውቅም በደስታ ወደ ፊት መራመዷን ቀጥላለች። “የኛ ችግር የምንይዘው ሸክም ሳይሆን የጸጥታ ስጋት ነበር” የምትለው ወጣቷ ባለፉት ዓመታት በኛ ላይ የደረሰው አስከፊ ሰቆቃና መከራ ለጠላትም እንዲገጥመው አልመኝም በማለት ትናገራለች። ባለፉት ዓመታት በአማራና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አዋሳኝ ወረዳዎች ሲከሰት የነበረው ግጭት የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች ለሞት፣ ለስደት፣ ለንብረት መውደም እንዲሁም ለተለያዩ ችግሮች ዳርጓቸው መቆየቱ የቅርብ ትውስታ ነው። አካባቢው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚገነባበት፣ ሰፋፊ የእርሻ ኢንቨስትመንት፣ የስኳር ፕሮጀክቶችና ሌሎች የኢንዱስትሪ ልማቶች ያሉበትና ለመተግበር የታቀደበት በመሆኑ የውጭ ሃይሎች ግጭት እንዲነሳ እጃቸውን ሊያስገቡ እንደሚፈልጉ ሳይታለም የተፈታ ነው። ወጣት ማሪማ ግጭት በተከሰተባቸው በነዚያ አስከፊ ጊዜያት የነበረውን ሁኔታ፣ የደረሰውን ጉዳት፣ በተከፈለው መስዋዕትነት የመጣውን ሰላም በሚያስታውስ የተስፋ ስሜት "ጸረ ሰላም ሃይሎች ያስነሱት ግጭት ለዘመናት በአንድነት የኖረውን የሁለቱ ክልሎች ህዝቦች ተስፋ አጨልሞት ነበር፤ በሰላም እጦት ሁሉም ህዝብ ጫካ ገብቶ ኑሮውን ከዱር አውሬ ጋር ያደረገበት የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው" ትላለች። በአሁኑ ወቅት ጸረ ሰላም ሃይሎችና ተባባሪዎቻቸው የፈጠሩት ሰው ሰራሽ ችግር ሊፈታ መቻሉ እፎይታን መፍጠሩን ትገልጻለች። በወቅቱ ሕክምና፣ መድሃኒትና ሌሎች የጤና መጠበቂያ ቁሶች ባለመኖራቸው ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በወባ እና ሌሎች በሽታዎች ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች እንዳሉ በመጥቀስ፤ በአሁኑ ወቅት የጸጥታ አካላትና ሰላም ፈላጊ የአካባቢው ተወላጆች ከመንግሰት ጋር በመሆን ባደረጉት ጥረት የነበረው ግጭት ተወግዶ በአካባቢው ሰላም ሰፍኗል። ይህም ለማሪማና ለአካባቢው ነዋሪዎች እፎይታን በማጎናጸፉ በጣም ደስተኛ ናቸው። የተገኘውን ሰላም ተከትሎ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማንዱራ ወረዳ ተነስታ በአማራ ክልል አዊ ዞን ቻግኒ ከተማ በመምጣት ለመገበያየት በቅታለች። ከጓደኞቿ ጋር ከቻግኒ ከተማ የሚፈልጉትን ገዝተው ወደ አካባቢያቸው ወስደው በትርፍ ለመሸጥ ምቹ ሁኔታም ተፈጥሮላቸዋል። በቻግኒ ከተማ የቅዳሜ ገበያ የተለያዩ የንግድ እንቅስቃሴዎች ይካሄዳሉ። በርበሬ፣ የተለያዩ የጥራጥሬ፣ የቅባትና የአገዳ ምርቶች ለሽያጭ ይቀርባሉ። አልባሳት፣ የሴቶች ጌጣጌጥ እና የንጽህና መጠበቂያ ቁሶች እንዲሁም ሌሎች የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ንግድ ልወውጥ የሚካሄድባት ከተማ መሆኗን በነበረኝ የአጭር ጊዜ ቆይታ አስተውያለሁ። ገበያተኛው የተፈጠረውን ሰላም በማጣጣም ላይ መሆኑን በገበያው ውስጥ ከሚያሳየው መስተጋብር መረዳት ቀላል ነው። እኔም ይሄን በተደጋጋሚ ታዝቢያለሁ። ከህዝቡ ፊት ያነበብኩት በግጭቱ የተነሳ በደረሰው ችግር ምክንያት ቁርሾና ቂም በቀል ውስጥ መግባትን ሳይሆን የሰላምና እርስ በርስ መዋደድና የመደጋገፍ ስሜትን ነው። ይሄን ደግሞ በቻግኒ ከተማ በሚካሄደው የቅዳሜ ገበያ መስተጋብር ላይ ተገኝቶ ማረጋገጥ ይቻላል። ገበያው የሁለቱም ክልሎች ህዝቦች ያላቸውን ይዘው መጥተው በነጻነት የሚገበያዩበት ነው። አሁን በሰላም ተገበያይቶ ወደ ቤት የሚመለስበት ሁኔታ በመፈጠሩ ለወጣት ማሪማ እና እንደ እሷ ላሉ ወጣቶች ደስታና እፎይታን ሰጥቷል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የማንዱራ ሚሊሻ የሆኑት አንመይ አልቤም በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም መታጣት ችግር ዛሬ መፈታት በመቻሉ በነጻነት ያለስጋት ለመገበያየት መብቃቱን አስረድቷል። "ያ አሰቃቂና የእልቂት ጊዜ አልፎ ተገናኝተንና እርስ በርስ ተገበያይተን በሰላም ወደየቤታችን እንመለሳለን ብሎ ማሰብ እንደ ከንቱ ህልም ነበር" ይላል የነበረውን ሁኔታ ሲያስታውስ። “ሚሊሻ እንደመሆኔ ከፌዴራልና ከክልሎች የጸጥታ ሃይሎች ጎን በመሰለፍ ግጭት ቀስቃሾችን ለመፋለም ጨካ ለጫካ ያሳለፍነው ጊዜ መቼም አይረሳኝም” ያለው ሚሊሻ አንመይ፣ ስንቶች በሕክምና፣ በመድሃኒትና ምግብ እጦት ህይወታቸው ማለፉን አንስቷል። "አማሟቴን አሳምረው" እንደሚባላው በወጉ መሞትና መቅበር ትልቅ ጸጋ መሆኑን የገለጸው አንዳች የሀዘን ስሜት ውስጥ በመግባት ነው። አሁን ላይ ሁሉም የደረሰውን ጉዳት በመርሳት የተገኘውን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል እየተንቀሳቀሰ ነው። የሁለቱ ክልል ህዝቦች ቂም በቀልን ትተን በጋራ የምንሰራበት ወቅት ላይ መድረሳችን ህዝቡ ከጥንት ጀምሮ ያለው የመተሳሰብ፣ የአብሮነትና አንድነት የመንፈሰ ጠንካራነት ማሳያ እንደሆነም ነው የገለጸው። በእርግጥም የማንዱራ ሚሊሻው እንዳለው በአካባቢያቸው ትምህርት ቤቶች በመከፈታቸው ህጻናት ያለስጋት በመማር ላይ ናቸው። የጤና ተቋማትም የተለመደውን የሕክምና አገልግሎት እየሰጡ ነው። በሰላም እጦት ተዘግተው የነበሩ መንገዶች በመከፈታቸውም ሁሉም ተሯሩጦ ኑሮውን ለማሸነፍ ላይ ታች እያለ ነው። ባለሃብቶችም በክረምቱ በግብርናው መስክ ተሰማርተው ማልማት ችለዋል። የጸጥታ ስጋት ተወግዶ ሌሎች የልማት ሥራዎች ሲተገበሩ ማየት ትልቅ ስኬት ነው። በአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የቻግኒ ከተማ ነዋሪ አቶ ሲራጅ አዲስ እንዳሉት ግጭት በነበረበት ወቅት በአካባቢው የኢንቨስትመንትና የንግድ እንቅስቃሴ ተዳክሞ ነበር። እሱ ቀርቶ በሰላም ውሎ ለማደር ጊዜው ከባድ ነበር ይላሉ። "የተገኘው ሰላም በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች እና በህብረተሰቡ የጋራ ጥረት በመሆኑ ሰላሙ አስተማማኝና ዘላቂ እንዲሆን ሁላችንም የበኩላችንን መወጣት ይኖርብናል" ብለዋል። አሁን ላይ ያለፈውን የመከራ ጊዜ፣ በሞት የተለየውን ወገን፣ የወደመውን ሀብትና ንብረት በመርሳት በተገኘው ሰላም በጋራ ሰርቶ ራስንና አካባቢውን ለመለወጥ መትጋት እንደሚገባ ነው የመከሩት። ያለፈን በደልና ቅሬታ በእርቅና በይቅርታ በማለፍ ነገን ብሩህ ለማድረግ መትጋት አለብን በማለትም ነው ያስገነዘቡት። አቶ ሲራጅ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት የጉሙዝ ማህበረሰብ ወደ ቻግኒ መጥቶ ያለውን ሽጦ የሚፈልገውንም ገዝቶ ይሄዳል፤ እነሱም ወደ መተከልና ማንዱራ በመሄድ ያላቸውን ይሸጣሉ፤ የፈለጉትንም ገዝተው የሚመጡበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። ይሄን አብሮነት በማጠናከር ሁለንተናዊ የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰላምን ማጽናት ላይ ጠንክሮ መስራት ይገባል። በአማራም ሆነ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ችግር ሲፈጥሩ የነበሩ ወንጀለኞችን አጋልጦ ለህግ ማቅረብ ያስፈልጋል። አሁንም የጥፋት ተልዕኮ ይዘው ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱትን አደብ እንዲገዙ ማድረግ ተገቢ ነው። ወንጀለኛን ለህግ አጋልጦ መስጠትን ከተለማመድን ነገም አካባቢውን የጦር ቀጣና ለማድረግ የሚፈልጉ የጥፋት ሃይሎች መግቢያ ቀደዳ አይኖራቸውም ይላሉ። ሃገር በአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን በሁሉም ዜጎች የተባበረ ክንድ ትገነባለች፤ ደህንነቷም ድንበሯም ይጠበቃል። ለዛሬው ትውልድ የደረሰችውም የብዙዎች ዋጋ ተከፍሎባት እንደመሆኑ በጋራ በሰላምና በአብሮነት ይሄንኑ ማስቀጠል የግድ ይላል። በተለይም የሰላም ጉዳይ ቅድሚያ ትኩረት የሚወስድ እንደመሆኑ አካበቢን የመጠበቅ የነቃ ተሳትፎን ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ ልታለማውና ልትጠቀምበት የምትችለው ገና ብዙ ያልሰራችበት ሃብት ባለቤት መሆኗ የአንዳንድ ሃይሎችን ቀልብ መሳቡ የሚጠበቅ ነው። ሰላሟ ሲረጋገጥ የዜጎች ደህንነት ሲከበር የተጀመረው የእድገት ጉዞ መፋጠኑ የማይቀር በመሆኑ ሁሉም የድርሻውን መወጣት ይኖርበታል።
ልዩ ዘገባዎች
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 156
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 312
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል።   “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል።   ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 470
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
የአንጋፋው የሥነ ጽሑፍ መምህርና ሐያሲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ
Mar 8, 2023 558
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 29/2015 የአንጋፋው የሥነ ጽሑፍ መምህርና ሐያሲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ።   በ1944ዓ.ም በደሴ ከተማ የተወለዱት ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው ከ1976ዓ.ም ጀምሮ ሕይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በተመራማሪነት በአማካሪነት፣ በትምህርት ክፍል ኃላፊነት በቦርድ አባልና እና በሌሎች የኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል። ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን ‹‹የሥነ ጽሑፍ መሰረታውያን›› እና ‹‹ከበዓሉ ግርማ እስከ አዳም ረታ›› እና ሌሎች ሶስት መጽሐፍትን አሳትመዋል፡፡   ስርዓተ ቀብራቸው በዛሬው እለት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ተከናውኗል። የአንጋፋው የስነ-ጽሑፍ ሰው ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው የአንድ ሴት ልጅና የሶስት ወንድ ልጆች አባት ነበሩ።
በብዛት የታዩ
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 2184
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 878
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
የካራማራ ድል የኢትዮጵያ ጦር በዜያድባሬ ጦር ላይ ታሪካዊ ገድል የፈጸመበት ነው ... በውጊያው የነበሩ የጦር መኮንኖች
Mar 5, 2021 841
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2013(ኢዜአ) የካራማራ ጦርነት ድል የኢትዮጵያ ጦር በሶማሊያ የወራሪው የዜያድባሬ ጦር ላይ ታሪካዊ ገድል የፈጸመበት ነው ሲሉ በአውደ ውጊያው ላይ የነበሩ የጦር መኮንኖች ገለጹ። ኢትዮጵያዊያን ለአገራቸው ሉዓላዊነት ሁልጊዜ ዘብ መቆም አለባቸው ብለዋል።  የካራማራ ጦርነት 43ኛ ዓመት የድል በዓል መታሰቢያ ዛሬ በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኩባ የወዳጅነት አደባባይ ተከብሯል። ሶማሊያን ለ21 ዓመታት ያስተዳደሩት ዚያድባሬ 'ታላቋን የሶማሊያ ሪፐብሊክ ለመመስረት' በሚል "ድንበራችን እስከ አዋሽ ይደርሳል" እያሉ በመዛት የጦርነት ነጋሪት መጎሰማቸው የሚታወስ ነው። ይሄን እውን ለማድረግ በ1969 ግልጽ ወረራ ኢትዮጵያ ላይ ፈጸሙ። የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም የኩባ ወታደሮችም የተሳተፉበት የኢትዮጵያ ጦር የእብሪተኛውን የዚያድባሬ ጦር ካራ ማራ ላይ ድል በማድረጉ የኢትዮጵያ አሸናፊነት በአደባባይ ታወጀ። በካራማራ ጦርነት በአውደ ውጊያው ላይ የነበሩ የቀድሞ የሠራዊት አባላት ብርጋዴል ጀኔራል ሃይለመለኮት ማሞ፣ ሻምበል ባሻ ሁሴን ጎበና እና መቶ አለቃ በቀለ በላይ ድሉን አስመልክቶ የምስክርነት ቃላቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። ጦርነቱ የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ የገባውን ወራሪውን የሶማሊያ ጦር ከአገር ለማስወጣትና ድል ለማድረግ የሕይወት መስዋዕትነት የተከፈለበት መሆኑንና ኢትዮጵያም በድሉ ክብሯ መጠበቁን ገልጸዋል። በምድርና በአየር ወራሪ የሶማሊያ ጦርን በመደምሰስ የኢትዮጵያ ሠራዊት ታሪካዊ፣ አስደናቂ ገድልና ጀብድ መፈጸሙንም ተናግረዋል። በወቅቱ የነበሩ የሠራዊቱ አባላት ሕይወቴ ከአገሬ አይበልጥም ብለው ያሳዩት ተጋድሎ የማይረሳ ነው ብለዋል የጦር መኮንኖቹ። ኢትዮጵያዊያን ሁልግዜ አገራቸውን ነቅተው መጠበቅ እንዳለባቸውና ለሉዓላዊነቷ ዘብ መቆም እንደሚገባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስ የካራማራው ጦርነት ኢትዮጵያ በውጭ ወራሪ ኃይል ላይ ያስመዘገበችው ድል መሆኑን ገልጸዋል። በጦርነቱ ላይ የኩባ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ወታደሮች ጎን በመሆን መዋጋታቸውንና 163 ኩባዊያን ወታደሮች የሕይወት መስዋዕትነት መክፈላቸውን ተናግረዋል። "የተገኘው ድል በኢትዮጵያና በኩባ ሕዝቦች መካከል ያለውን የወንድማማችነት ትስስር የሚያሳይ ምስክር ነው" ብለዋል። "ኢትዮጵያና ኩባን ከ43 ዓመት በፊት ያስተሳሰረ የወዳጅነትና ትብብር መንፈስ አሁንም አለ" ያሉት አምባሳደር ቪልማ፤ አገራቱ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማጠናከር እየሰሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የደቡብ አሜሪካና ካሪቢያን አገሮች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ቤኩማ መርዳሳ ፣ "የካራማራ ድል ኢትዮጵያዊያን የዚያድ ባሬ ወራሪ ኃይል በኢትዮጵያ ላይ የፈጸመውን ወረራ በመመከት ድል የተጎናጸፉበት ታሪክ ነው" ብለዋል። ድሉ ኢትዮጵያ ወራሪ ሃይልን በማሸነፍ ዳግም ነጻነቷን ያወጀችበትና ኢትዮጵያዊያን የሕይወት መስዋዕትነት ከፍለው ሉዓላዊነታቸውን ያስጠበቁበት እንደሆነም አክለዋል። ኩባ በጦርነቱ ወቅት ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም ያሳየችው አጋርነት ኢትዮጵያ ሁሉጊዜ የምታወሳውና የምትዘክረው እንደሆነም አመልክተዋል። የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አበበ አያሌው ማህበሩ በአጥንትና በደም የተሳሰረውን የኢትዮጵያና ኩባ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን ተናግረው፤ ኩባ ከኢትዮጵያ ጎን ሆና ላሳየችው አጋርነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።  የሰብአዊ መብት ተሟጋች አቶ ታማኝ በየነ "የካራማራ ድል ኢትዮጵያዊያን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ኢትዮጵያን ያቆዩበት ታሪካዊ ገድል ነው" ብለዋል። ኢትዮጵያዊያን በታሪክ ከተገኙ ድሎች በመማር አሁንም ቢሆን ከልዩነታቸው ይልቅ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም አገራቸውን መጠበቅ እንደሚገባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊያን ሁልጊዜም ታሪክ ለሰሩ ወታደሮችና የጦር ሠራዊት አባላት ክብር መስጠት አለባቸው ብለዋል። በኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት አደባባይ በተከበረው የድል በዓል የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስን ጨምሮ የተለያዩ አካላት በጦርነቱ ለተሰው ጀግኖች የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። ከኢትዮጵያዊያን የየካቲት ወራት ድሎች አንዱ የሆነው የካራማራ ድል 43ኛ ዓመቱን አስቆጥሮ የድል በዓሉ በኢትዮጵያዊያን ዛሬም እየተከበረ ይገኛል።
ባለፉት ስድስት ወራት በሀገራዊ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ላይ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ ተሰርቷል--የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Mar 4, 2023 709
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 25 ቀን 2015 በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት በአገራዊ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ላይ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ መከናወኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተዘጋጀው የፌዴራልና ክልል ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ኢትዮጵያ በጫናዎች ውስጥ ሆናም በተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ተመዝግቧል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት፣ በመልካም አስተዳደር ሥራዎች፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች አበረታች ውጤት ተገኝቷል ብለዋል። ሰላምና መረጋጋትን በማስፈን በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እንደ አገር የተመዘገቡ ስኬቶች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ ለእነዚህ ስኬቶች የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን አስተዋፅኦ ድርሻ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። በመንግስት እና ሕወሓት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት እንዲዝ እንዲሁም በሌሎች አገራዊ ስኬቶች ላይ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ጠንካራ ስራ አከናውኗል ነው ያሉት። "በኢትዮጵያ አክራሪነትና ጽንፈኝነት ውስብስብ ችግሮችን በመፍጠር ተጽእኖ አሳድረዋል" ሲሉ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይሄንን በመመከትም አበረታች ስራ መሰራቱን አመልክተዋል። "የዜጎች ሰላም ወጥቶ በሰላም መመለስ እረፍት የሚነሳቸው የውስጥና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ለማመስ የሚያደርጉትን እኩይ ሙከራ ማክሸፍ ይገባል" ብለዋል። "ኢትዮጵያ የሚያጋጥሟትን ፈተናዎች በድል ተወጥታ የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ እውን እንድታደርግ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በተናበበ አኳኋን መምራት የሚጠበቅብን ወቅት ላይ ደርሰናል" ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በዲሞክራሲያዊ ሽግግር ላይ መሆኗን የገለጹት ዶክተር ለገሰ፤ ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ በዘርፉ የሚከናወኑት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። በቀጣይም አክራሪነትና ፅንፈኝነትን በቅንጅት በመመከት የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚመጥን የሚዲያ እና ኮምኒኬሽን ስራ መስራት እንደሚገባም ሚኒስትሩ አሳስበዋል።    
በብዛት የታዩ
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 2184
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 878
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
የካራማራ ድል የኢትዮጵያ ጦር በዜያድባሬ ጦር ላይ ታሪካዊ ገድል የፈጸመበት ነው ... በውጊያው የነበሩ የጦር መኮንኖች
Mar 5, 2021 841
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2013(ኢዜአ) የካራማራ ጦርነት ድል የኢትዮጵያ ጦር በሶማሊያ የወራሪው የዜያድባሬ ጦር ላይ ታሪካዊ ገድል የፈጸመበት ነው ሲሉ በአውደ ውጊያው ላይ የነበሩ የጦር መኮንኖች ገለጹ። ኢትዮጵያዊያን ለአገራቸው ሉዓላዊነት ሁልጊዜ ዘብ መቆም አለባቸው ብለዋል።  የካራማራ ጦርነት 43ኛ ዓመት የድል በዓል መታሰቢያ ዛሬ በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኩባ የወዳጅነት አደባባይ ተከብሯል። ሶማሊያን ለ21 ዓመታት ያስተዳደሩት ዚያድባሬ 'ታላቋን የሶማሊያ ሪፐብሊክ ለመመስረት' በሚል "ድንበራችን እስከ አዋሽ ይደርሳል" እያሉ በመዛት የጦርነት ነጋሪት መጎሰማቸው የሚታወስ ነው። ይሄን እውን ለማድረግ በ1969 ግልጽ ወረራ ኢትዮጵያ ላይ ፈጸሙ። የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም የኩባ ወታደሮችም የተሳተፉበት የኢትዮጵያ ጦር የእብሪተኛውን የዚያድባሬ ጦር ካራ ማራ ላይ ድል በማድረጉ የኢትዮጵያ አሸናፊነት በአደባባይ ታወጀ። በካራማራ ጦርነት በአውደ ውጊያው ላይ የነበሩ የቀድሞ የሠራዊት አባላት ብርጋዴል ጀኔራል ሃይለመለኮት ማሞ፣ ሻምበል ባሻ ሁሴን ጎበና እና መቶ አለቃ በቀለ በላይ ድሉን አስመልክቶ የምስክርነት ቃላቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። ጦርነቱ የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ የገባውን ወራሪውን የሶማሊያ ጦር ከአገር ለማስወጣትና ድል ለማድረግ የሕይወት መስዋዕትነት የተከፈለበት መሆኑንና ኢትዮጵያም በድሉ ክብሯ መጠበቁን ገልጸዋል። በምድርና በአየር ወራሪ የሶማሊያ ጦርን በመደምሰስ የኢትዮጵያ ሠራዊት ታሪካዊ፣ አስደናቂ ገድልና ጀብድ መፈጸሙንም ተናግረዋል። በወቅቱ የነበሩ የሠራዊቱ አባላት ሕይወቴ ከአገሬ አይበልጥም ብለው ያሳዩት ተጋድሎ የማይረሳ ነው ብለዋል የጦር መኮንኖቹ። ኢትዮጵያዊያን ሁልግዜ አገራቸውን ነቅተው መጠበቅ እንዳለባቸውና ለሉዓላዊነቷ ዘብ መቆም እንደሚገባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስ የካራማራው ጦርነት ኢትዮጵያ በውጭ ወራሪ ኃይል ላይ ያስመዘገበችው ድል መሆኑን ገልጸዋል። በጦርነቱ ላይ የኩባ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ወታደሮች ጎን በመሆን መዋጋታቸውንና 163 ኩባዊያን ወታደሮች የሕይወት መስዋዕትነት መክፈላቸውን ተናግረዋል። "የተገኘው ድል በኢትዮጵያና በኩባ ሕዝቦች መካከል ያለውን የወንድማማችነት ትስስር የሚያሳይ ምስክር ነው" ብለዋል። "ኢትዮጵያና ኩባን ከ43 ዓመት በፊት ያስተሳሰረ የወዳጅነትና ትብብር መንፈስ አሁንም አለ" ያሉት አምባሳደር ቪልማ፤ አገራቱ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማጠናከር እየሰሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የደቡብ አሜሪካና ካሪቢያን አገሮች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ቤኩማ መርዳሳ ፣ "የካራማራ ድል ኢትዮጵያዊያን የዚያድ ባሬ ወራሪ ኃይል በኢትዮጵያ ላይ የፈጸመውን ወረራ በመመከት ድል የተጎናጸፉበት ታሪክ ነው" ብለዋል። ድሉ ኢትዮጵያ ወራሪ ሃይልን በማሸነፍ ዳግም ነጻነቷን ያወጀችበትና ኢትዮጵያዊያን የሕይወት መስዋዕትነት ከፍለው ሉዓላዊነታቸውን ያስጠበቁበት እንደሆነም አክለዋል። ኩባ በጦርነቱ ወቅት ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም ያሳየችው አጋርነት ኢትዮጵያ ሁሉጊዜ የምታወሳውና የምትዘክረው እንደሆነም አመልክተዋል። የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አበበ አያሌው ማህበሩ በአጥንትና በደም የተሳሰረውን የኢትዮጵያና ኩባ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን ተናግረው፤ ኩባ ከኢትዮጵያ ጎን ሆና ላሳየችው አጋርነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።  የሰብአዊ መብት ተሟጋች አቶ ታማኝ በየነ "የካራማራ ድል ኢትዮጵያዊያን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ኢትዮጵያን ያቆዩበት ታሪካዊ ገድል ነው" ብለዋል። ኢትዮጵያዊያን በታሪክ ከተገኙ ድሎች በመማር አሁንም ቢሆን ከልዩነታቸው ይልቅ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም አገራቸውን መጠበቅ እንደሚገባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊያን ሁልጊዜም ታሪክ ለሰሩ ወታደሮችና የጦር ሠራዊት አባላት ክብር መስጠት አለባቸው ብለዋል። በኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት አደባባይ በተከበረው የድል በዓል የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስን ጨምሮ የተለያዩ አካላት በጦርነቱ ለተሰው ጀግኖች የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። ከኢትዮጵያዊያን የየካቲት ወራት ድሎች አንዱ የሆነው የካራማራ ድል 43ኛ ዓመቱን አስቆጥሮ የድል በዓሉ በኢትዮጵያዊያን ዛሬም እየተከበረ ይገኛል።
ባለፉት ስድስት ወራት በሀገራዊ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ላይ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ ተሰርቷል--የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Mar 4, 2023 709
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 25 ቀን 2015 በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት በአገራዊ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ላይ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ መከናወኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተዘጋጀው የፌዴራልና ክልል ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ኢትዮጵያ በጫናዎች ውስጥ ሆናም በተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ተመዝግቧል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት፣ በመልካም አስተዳደር ሥራዎች፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች አበረታች ውጤት ተገኝቷል ብለዋል። ሰላምና መረጋጋትን በማስፈን በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እንደ አገር የተመዘገቡ ስኬቶች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ ለእነዚህ ስኬቶች የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን አስተዋፅኦ ድርሻ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። በመንግስት እና ሕወሓት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት እንዲዝ እንዲሁም በሌሎች አገራዊ ስኬቶች ላይ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ጠንካራ ስራ አከናውኗል ነው ያሉት። "በኢትዮጵያ አክራሪነትና ጽንፈኝነት ውስብስብ ችግሮችን በመፍጠር ተጽእኖ አሳድረዋል" ሲሉ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይሄንን በመመከትም አበረታች ስራ መሰራቱን አመልክተዋል። "የዜጎች ሰላም ወጥቶ በሰላም መመለስ እረፍት የሚነሳቸው የውስጥና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ለማመስ የሚያደርጉትን እኩይ ሙከራ ማክሸፍ ይገባል" ብለዋል። "ኢትዮጵያ የሚያጋጥሟትን ፈተናዎች በድል ተወጥታ የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ እውን እንድታደርግ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በተናበበ አኳኋን መምራት የሚጠበቅብን ወቅት ላይ ደርሰናል" ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በዲሞክራሲያዊ ሽግግር ላይ መሆኗን የገለጹት ዶክተር ለገሰ፤ ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ በዘርፉ የሚከናወኑት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። በቀጣይም አክራሪነትና ፅንፈኝነትን በቅንጅት በመመከት የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚመጥን የሚዲያ እና ኮምኒኬሽን ስራ መስራት እንደሚገባም ሚኒስትሩ አሳስበዋል።    
የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂና በስትራቴጂ የታገዘ ስራ እየተከናወነ ነው -ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ
Mar 3, 2023 645
ባህር ዳር (ኢዜአ) የካቲት 24/2015 የግብርናው ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂና በስትራቴጂ የታገዘ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለ አስታወቁ። የክልሉ ግብርና ቢሮ ዛሬ 241 የእርሻ ትራክተሮችን ለአርሶ አደሮች አስረክቧል። ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ በወቅቱ እንደገለጹት ባለፉት አመታት ለግብርናው ዘርፍ ትኩረት የተሰጠ ቢሆንም አሰራሩ የአርሶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ በኩል ለውጥ ሳይመጣ ቆይቷል። የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂና በስትራቴጂ የታገዘ ስራ እየተከናወነ ነው። ከቅርብ አመታት ወዲህ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት በተግባር የታገዘ ለውጥ የሚያመጣ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በስንዴና አኩሪ አተር ምርት በክልሉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል። የክልሉ መንግስት የአርሶ አደሩን ጊዜ የሚቆጥቡና የምርት ብክነትን የሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎችን በረጅም ጊዜ የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። አርሶ አደሩን በቴክኖሎጂ የማዘመንና በረጅም ጊዜ ክፍያ የቴክኖሎጂ ግብዓቶች እንዲያገኝ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። በግብርናው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት በተለመደው መንገድ መሄድ እንደማያዋጣ የገለጹት ደግሞ የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ ናቸው። የግብርና ምርታማነትን በፍጥነት ለማሳደግ ዘመኑ ያፈራቸውን ጊዜ ቆጣቢና የአርሶ አደሩን ድካም የሚቀንሱ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። ባለፉት ዓመታት መንግስት የግብርናውን ዘርፍ የሚያዘምኑ ውሳኔዎችን በማስተላለፍ የእርሻ ቴክኖሎጂዎች ከቀረጥ ነጻ እያስገባ መሆኑን ተናግረዋል። በሃገር አቀፍ ደረጃ ቴክኖሎጂን ተጠቅሞ ምርታማነትን በማሳደግ በኩል ብዙ እንደሚቀር የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ከሚታረሰው መሬት 22 በመቶው ብቻ በትራክተር እየታረሰ መሆኑን ገልጸዋል። አርሶ አደሩ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆን አስቻይ ሁኔታዎች መቅደም እንዳለባቸው አመልክተው፤ ለዚህም አንዱና ዋነኛው መሬትን በኩታ ገጠም ማረስ እንደሆነ አብራርተዋል። ለዚህም ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆናቸውን የተናገሩት ዶክተር ግርማ፤ አሁን ላይ እንደ ሀገር 6 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም ተደራጅቷል ብለዋል። ''አርሶ አደሩ በቴክኖሎጂ ተደራሽ እንዲሆን በማድረግ ምርታማነትን ለማሳደግ ሰፊ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው'' ያሉት ደግሞ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኃይለማሪያም ከፍያለው ናቸው። በክልሉ ለዓመታት የነበሩት ትራክተሮች ከ800 ያልበለጡ እንደነበሩ አስታውሰው፣ ባለፉት ሁለት ዙሮች ብቻ ከ700 በላይ ትራክተሮች ለአርሶ አደሮች ማስረከብ ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ በዘር በመሸፈን ላይ ከሚገኘው 4 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር የእርሻ መሬት 11 በመቶው ብቻ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሚታረስ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም ለአርሶ አደሮች ትራክተሮችን የማቅረብና ሌሎች የማዘመን ጅምር ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የክልሉ መንግስት በረጅም ጊዜ ክፍያ የትራክተር ባለቤት እንዲሆኑ ማድረጉ እንዳስደሰታቸው የገለጹት ደግሞ ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን ደንብያ ወረዳ የመጡት አርሶ አደር አሰፋ አያሌው ናቸው። አርሶ አደሮቹ የተረከቧቸው የእርሻ ትራክተሮች የተለያየ የፈረስ ጉልበት እንዳላቸው ተገልጿል። በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የክልሉና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም አርሶ አደሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት ከብልሹ አሰራርና ሌብነት ጋር በተያያዘ ከ200 በላይ አመራርና ሰራተኞች ላይ ክስ ተመስርቷል"-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Feb 26, 2023 642
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 ባለፉት ስድስት ወራት ከብልሹ አሰራርና ሌብነት ጋር በተያያዘ ከ200 በላይ አመራርና ሰራተኞች ላይ ክስ መመስረቱን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ተጠናቋል። በማጠቃለያው ወቅት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ብልሹ አሰራርና ሌብነትን የመከላከል ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አገልግሎት አሰጣጥን ከወቅቱ ጋር እንዲሄድ ለማስቻል በርካታ ዘርፎችን የማዘመን እና የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት ጫናን በመቀነስ የነዋሪውን ችግር እንዲያቀሉ የተጀመሩት የእሁድ ገበያ እና የሌማት ትሩፋት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ጠቁመዋል። በእሁድ ገበያ ለመሰረታዊ ፍጆታ የሚሆኑ ምርቶች በቀላሉ ህብረተሰቡ ጋር እንዲደርሱ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል። አስተዳደሩ ከተማዋን ለነዋሪዎች ጽዱ፣ ውብና ምቹ ከማድረግ ባሻገር ዓለም አቀፍ የዲፕሎማቲክ ከተማነቷን የምትመጥን ለማድረግ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ተግባራዊ እያደረገ ነውም ብለዋል። “ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከር አመራራችን ፅንፈኝነትን፣ ጥላቻን፣ የህብረተሰቡን አንድነት የሚንዱ አስተሳሰቦችን፣ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚደረጉ የሚዲያ ዘመቻዎችንና ሌሎች የፓርቲያችን እሳቤ ያልሆኑ አመለካከቶችን በመዋጋት ረገድ እየተሰራ መሁኑ ተናግረዋል። “አሁንም ወደ ከተማ የሚደረገው ፍልሰት እና በህቡእ አደረጃጀት የሚደረግ ህገ-ወጥነት ላይ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል” ሲሉ መግለጻቸውን ከንቲባ ጽህፈት ቤት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያሰፈረው መረጃ ያመለክታል። በቀሪ የበጀት አመቱ ወራት ያልተከናወኑ ተግባራት ተለይተው በእቅድ ክለሳ እንዲካተቱ በማድረግ የህዝቡን ኑሮ የሚያቀሉ ፕሮጀክቶች ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት እንደሚሰሩም ከንቲባ አዳነች አክለው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በፈረንሳይኛና ትግሪኛ ቋንቋዎች መረጃዎችን ተደራሽ የሚያድረግ ድረ-ገጽ አስጀመረ
Mar 4, 2023 610
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 25/2015፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ መረጃዎችን በፈረንሳይኛና ትግሪኛ ቋንቋዎች ተደራሽ የሚያደርግ አዲስ ድረ-ገጽ አስጀመረ። አዲሱን ድረ-ገጽ በይፋ ስራ ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ትዕግስት ሀሚድ ናቸው። የተቋሙ ዌብ አድሚኒስትሬተር ሄኖክ አብይ በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት አዲሱ ድረ-ገጽ መረጃዎችን በተለያዩ ቋንቋዎች በእኩል ጥራት ለማድረስ የሚያስችል ሆኖ የተገነባ ነው።   የተቋሙን ብራንድ መሰረት ባደረገ መልኩ የተዘጋጀው ድረ-ገጹ ከመረጃ ጥራትና ደኅንነት አንጻርም አስተማማኝ ሆኖ አገልግሎት እንዲሰጥ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አማካኝነት መገንባቱንም ገልጸዋል። ድረ-ገጹ ከዚህ ቀደሞ በተቋሙ ሲሰራባቸው የነበሩትን እንግሊዝኛ ፣ አረብኛ ፣ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞን ጨምሮ በአዲስ መልኩ በቅርቡ የተጀመሩትን ፈረንሳይኛና ትግሪኛ ቋንቋዎችን በማካተት አገልግሎት እንዲሰጥ ሆኖ መደራጀቱን አስታውቀዋል። የኢዜአ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ እንዳሉት ኢዜአ የኢትዮጵያን ገጽታ የሚገነቡ ሀገራዊ ጉዳዮችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ተደራሽ የሚያደርጉ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ። አሁን ይፋ የሆነው አዲስ የድረ-ገጽ ይሀንኑ አላማ ለማስፈጸም የሚያግዝ ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚው አስተማማኝነቱና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኖ ዘመናዊ አገልግሎት ማቅረብ እንዲያስችል በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር መገንባቱን ተናግረዋል። በቀጣይም ኢዜአ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዘርፉ ልማት ዙሪያ የሚያከናውናቸውን ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው ተቋማቸው የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከኢዜአ ጋርም በዘርፉ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን ለመከላከል በጋራ ከመስራት ባለፈ በቀጣይም በዚህና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ግንኙነት የሚያሳድጉ ተግባራትን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። በድረ-ገጹ የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።  
የኢትዮጵያ የእቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማኅበር የአሰልጣኞች ሥልጠና የወሰዱ ባለሙያዎችን አስመረቀ
Mar 7, 2023 594
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 28/2015 የኢትዮጵያ የእቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማኅበር በ4ኛ ዙር የአሰልጣኞች ሥልጠና የወሰዱ 28 ባለሙያዎችን አስመረቀ። የአሰልጠኞች ሥልጠና የወሰዱት ሰልጣኞች በቀጣይ ዓለም አቀፍ የእቃ አስተላላፊዎች ሥልጠና /ፊያታ ዲፕሎማ/ መስጠት የሚያስችላቸው መሆኑ ተመላክቷል።   የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በሎጅስቲክ ዘርፍ የአገልግሎት ልህቀት አነስተኛው መስፈርት ነው። ከዘርፉ ፈተናዎችም ዋነኛው የአቅም ውስንነት መሆኑን ገልጸው የሚከሰቱት ዝቅተኛ አፈጻጸሞች ከዚሁ የመነጨ መሆኑን አንስተዋል። ባለሥልጣኑ ይህንን ለመቅረፍ ከተቋማት አደረጃጀት ጀምሮ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ማሳደግና የመሳሰሉ ሥራዎችን እየሰራ ነው ብለዋል። በዛሬው እለት የተመረቁ ሠልጣኞች በዘርፉ ያለውን ማነቆ በመፍታት በኩል ቁልፍ ሚና እንደሚኖራቸው ተናግረዋል። ሰልጣኞች በቆይታቸው ያገኙትን እውቀት ተግባራዊ በማድረግ ዘርፉን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ሊያግዙ እንደሚገባ አመላክተዋል።   የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ኤልሳቤት ጌታሁን በበኩላቸው በሎጅስቲክ ዘርፍ ያለው የአቅም ውስንነት ዘርፉ እንዳያድግ ማድረጉን ገልጸዋል። በንግድ ሥርዓት ውስጥ ሎጂስቲክ ዋነኛው መሆኑን ገልጸው በዘርፉ ያለውን የአቅም ውስንነት መቅረፍ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።   የዘርፉን አቅም ለማሳደግ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየሰጠ መሆኑን በመጠቆም። ማኅበሩ እስካሁን 200 ሰልጣኞች ዓለም አቀፍ የፊያታ ዲፕሎማ እንዲያገኙ ማድረጉንና 140 ባለሙያዎችን ደግሞ ለዓለም አቀፍ አሰልጣኝነት ማብቃቱን ገልጸዋል።
መጣጥፍ
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 447
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ)
Jan 25, 2023 487
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ) አየለ ያረጋል (ኢዜአ) መዳረሻዬ ሽሬ እንዳስላሴ ነው። ለዘገባ ሥራ ከባህርዳር- ጎንደር- ደባርቅ- ሸሬ መንገድ ከሚዲያ ባልደረቦች ጋር እየተጓዝኩ ነው። የጥምቀት ሙሽራዋ ጎንደር እየተኳኳለች ነበር። ደባርቅ ከመድረሴ በፊት ዳባት ትገኛለች-የደጃች አያሌው ብሩ ቁርቁር ከተማ። ደጃች አያሌው ትውልዳቸው በጌምድር ጋይንት ቢሆንም ግዛታቸውና ኑሯቸው ዳባት ነበር። ሞገደኛው ደጃዝማች አያሌው ብሩ በጎንደር ማኅበረሰብ ዘንድ ዝናቸው የናኘ ነው። ደጃዝማች አያሌው በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ (ከልጅ ኢያሱ እስከ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ-መንግሥት) ታሪካዊ ክንውኖች ጉልህ ተሳትፎ አላቸው። አንዷን ብቻ ልምዘዝ። ራስ ተፈሪ ‘ንጉሠ-ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ’ ደጃች አያሌው የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ ጉግሳ ወሌ ብጡልን (የንግሥት ዘውዲቱን ባለቤት) ወግተው የጎንደር ግዛት ‘ራስ’ ተብለው ለመሾም ቃል ቢገባላቸውም፤ ተልዕኳቸውን ተወጥተው ቃሉ ባለመፈጸሙ ደጃዝማቹ ከአጼው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። በዚህም:- "አያሌው ሞኙ፣ ሰው አማኙ ሰው አማኙ፣ የአያል ጠመንጃ፣ ስሟን እንጃ ስሟን እንጃ…” በማለት የጎንደር አዝማሪ አዚሟል። ዛሬም ይህ ግጥም የብዙ ባህላዊ ዘፈኖች አዝማች ነው። ደጃች አያሌው ብሩ ደፋር ናቸው ይባላል። ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር ቢቀያየሙም በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ሲመጣ ቅድሚያ ለአገሬ ብለዋል። ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘው የዶክተር ሀራልድ ናይስተሮም (ትርጉም ገበየሁ ተፈሪ እና ደሳለኝ አለሙ) መጽሐፍ እንደተጠቀሰው ደጃች አያሌው “ንጉሡ እንደኛ ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሁላችንም ናት" ብለው ጦራቸውን መርተው በሽሬ ግንባር ዘምተዋል። ጉዟችን ቀጥሏል። ደባትን እያለፍን ነው። ‘እንኳን ደህና መጡ፤ ወደ ጭና ታሪካዊቷ ሥፍራ’ የምትለዋን ታፔላን በስተግራ እያየን ወደ ደባርቅ ገሰገስን። የሰሜን ተራሮች የብርድ ወጨፎ ያረሰረሳትን ደባርቅን ከማለፋችን ሊማሊሞ ጠመዝማዛ ቁልቁለት ተቀበለን። አስፈሪ የሊማሊሞ መልክዓ ምድር የደጋው ሰሜን ውርጭ እና የተከዜ በርሃ ኬላ ነው። ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህን “የሰማይ የምድሩ ኬላ፣ የየብስ የጠፈሩ ዋልታ አይበገር የዐለት ጣራ፣ አይመክተው መከታ ሊማ-ሊሞ አድማስ ሰበሩ፣ በጎማ ፈለግ ይፈታ? በትሬንታ እግር ይረታ?…” ብሎ የመኪና መንገድ ተገንብቶበት በማየቱ ግርምቱን የተቀኘለትም ለዚህ ይመስላል። ከሊማሊሞ ቁልቁለት በኋላ አዲ-አርቃይ፣ ዛሪማ፣ ማይፀብሪ እና ሌሎች የጠለምት ወረዳ ከተማዎችን አልፈን፤ የዋልድባ ረባዳማ አካባቢዎችን ተሻግረን ተከዜ ወንዝ ደረስን። የዚህን መንገድ እና ተከዜ ወንዝን ሳስብ የሀዲስ ዓለማየሁ ትዝታ አስተከዘኝ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር የወገንን ጦር ፊት ለፊት መቋቋም ሲሳነው በሰው ልጆች ላይ ተደርጎ የማያውቅ መርዝ በጅምላ የፈጀበት አሳዛኝ ታሪክ ነበር። በተከዜ ወንዝ ውሃን በመመረዝ የወገን ጦር ያለቀበት ሥፍራ ነው። የተከዜ ሸለቆ በኢትዮጵያዊያን ደምና አጥንት ዋጋ የተከፈለበት ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በአንድ ዕለት የተመለከቱትን እንዲህ ጽፈውታል። “የተከዜ ውሀ እመሻገሪያው ላይ ሰፊና ፀጥ ያለ ነው። ታዲያ ያ ሰፊ ውሀ፤ ገና ከሩቅ ሲያዩት ቀይ ቀለም በከባዱ የተበጠበጠ ይመስላል። “ምን ነገር ነው፤ ምን ጉድ ነው?” እየተባባልን ቀረብ ስንል መሻገሪያው በቁሙም በወርዱም ከዳር እስከ ዳር ሬሳ ሞልቶበት የዚያ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው። የሰው ሬሳ፣ የፈረስ እና የበቅሎ ሬሳ፣ ያህያ ሬሳ፣ ያውሬ ሬሳ፥ ሬሳ ብቻ! እግር ከራስ ራስ ከእግር እየተመሰቃቀለ እየተደራረበ ሞልቶበት፥ የዚያ ሁሉ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው”። ይሉናል። ቀጥለውም “በእውነቱ እንዲህ ያለውን መሳሪያ ምንም ጠላት ቢሆን በሰው ላይ ለማዋል የሚጨክን ሰው፥ ሰብዓዊ ስሜት የሌለው፣ አለት ድንጋይ የተፈጠረበት መሆን አለበት፤ እንዲህ ያለውን መሳሪያ በሰው ላይ ማዋል ሰብዓዊ ህሊና ሊሸከመው የማይችል እጅግ ከባድ መሆኑን ዓለም ሁሉ ያወቀውና ያወገዘው በመሆኑ የኢጣሊያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ከማድረጉ በቀር “ሌላ መንግሥት በሌላ አገር ላይ አደረገ’ ሲባል ተሰምቶ የሚያውቅ አይመስለኝም” ብለዋል። ከተከዜ ባህር ማዶ ጉዞዬ ያገኘኋት ሌላዋ ታሪካዊ ሥፍራ እንዳባጉና ናት። እንዳባጉና የወገን ጦር ትልቅ ገድል የፈጸመበት ነው። ጀግኖች አባቶቻችን የጠላት ታንክ ሳያስፈራቸው የጠላት ጅምላ ጨራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ተቋቁመው ጠላትን ድባቅ የመቱበት፤ ወደ አክሱም እንዲያፈገፍግ ያደረጉበት ሥፍራ ነው። “የጠላት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በጦር ሜዳው ትንንሽ ቦምቦች አውቶማቲክ ጠመንጃ ይተኩስ ነበር። አቢሲኒያኖች ደግሞ ከጠላት ጋር ግብግብ ገጥመው ጉዳይም አልሰጡትም ነበር…” ይላል ዶክተር ሀራልድ ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘ መጽሐፉ። ይህ አካባቢ በሀገር ፍቅር የነደዱ ኢትዮጵያዊያን ደም ያፈሰሱበት፣ አጥንት የከሰከሱበት፤ ለኢትዮጵያ መስዕዋትነት የከፈሉበት ነው። ይህ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ቀጣና ነው። ቀኑ ተገባዷል። ጉዟችን እንደቀጠለ ነው። እኔም የማሽላ ማሳዎችን ግራ ቀኝ እየተመለከትኩ ለዕለቱ መዳረሻችን ወደሆነችው ሽሬ ከተማ ገባን። ሽሬ በትግርኛ ‘ሽረ’ ሲሉት ይደመጣሉ። በእርግጥ ሽሬን ለመጀመሪያ ጊዜ መርገጤ ነው። ዕለቱም ጥር ሥላሴ ነው። ሽሬ በጥር ሥላሴ ትደምቃለች፤ ሙሉ ስሟም ሽረ እንዳስላሴ ነው። የሽሬ ሥላሴ ጠበል ሽሬ ደርሰን ማረፊያችንን ያዝን። ጊዜው በጣም አልመሸምና ከተማዋን በቀላሉ መቃኘት ይቻላል። ሽሬ ሰፊና ደማቅ የዞን ከተማ ናት። ከመካከላችን የአንደኛው ባለሙያ ቤተሰቦች ሽሬ ነበሩና አስጠሩን። ለሥላሴ ጠበል ግብዣ። ባል እና ሚስቱ ከልክ በላይ መስተንግዶ አደረጉልን። ‘ጠብ እርግፍ አድርገው አስተናገዱን’ ማለት ይቀላል። እንግዳ መቀበል ነባር ኢትዮጵያዊ እሴታችን ቢሆንም ጦርነት ውስጥ ለቆየ አካባቢ የተለየ መልክ ነበረው። እንግዳ አቀባበላቸው በእርግጥም የመሃል አገር ሰው የናፈቃቸው ይመስላል። የተትረፈረፈ እህልና ውሃ አቅርበው በ’ብሉልን፤ ጠጡልን’ ተማጽኗቸው የተነፋፈቀ ቤተ-ዘመድ ግብዣ አስመሰሉት። የሥላሴው ጠበል የሸሬ ጠላ ቀረበ። የሸሬ ጠላ ሳስታውስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ታወሱኝ። የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምሀሩ ፕሮፌሰር ሽብሩ በዘመነ ደርግ በዕድገት በሕብረት ዘመቻ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ሽሬ ዘምተው ነበር። በወቅቱ ታዲያ የሸሬ ጠላ ፍቅር ይዟቸው በየጊዜው ሲኮመኩሙ የተመለከቱ ሰዎች ‘ፕሮፌሰሩ ከጠፉ የሚገኙት ጠላ ቤት ነው’ ሲባሉ እንደነበር ‘ከጉሬ ማርያም እስከ አዲስ አበባ’ በተሰኘው ግለ ታሪካቸው አስፍረዋል። ከግብዣ መልስ ከማረፊያ ሆቴል ላይ ሆኜ ከተማዋን ስቃኛት ከጦርነት ድባቴ የተላቀቀች ይመስላል። የአመሻሽ ሕዝቡ እንቅስቃሴም ሆነ እስከ ሌሊቱ አጋማሽ የሚሰሙ የመዝናኛ ቤቶች ሙዚቃዎች የከተማዋን አሁናዊ መልክ የገለጠልኝ ነበር። ንጋት ላይ በቁርስና ቡና ሰዓታት ከሰዎች ጋር መስተጋብሬ ጀመረ። በጦርነት አዙሪት የከረመችው ሽሬና አካባቢው ኑሮ እጅጉን የከበደ ነበር። መልከ-ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች አስተናግደዋል። አሁናዊ ምላሻቸው “ተመስገን፤ ያ ሁሉ አለፈ” የሚል ነው። ገበያው ተረጋግቷል፤ ማህበራዊ ኑሮ ተመልሷል። ድህረ-ሰላም ስምምነት ለሽሬ ነዋሪዎች ሁለንተናዊ እፎይታን አንብሯል። ከቀናት በኋላ በአክሱም የታዘብኩትም እንዲህ ነው። ኑሮን ያቀለለው የተቋማት አገልግሎት ጅማሮ በመጀመሪያ ዘገባ ስራዬ መሰረተ ልማትን አገልግሎት ቃኘሁ። ባንክ፣ ቴሌ፣ ሆስፒታል… መሰሎቹን። ተጠቃሚዎችንም፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ስራ ሃላፊዎችንም አነጋገርሁ። ከሰላም ስምምነቱ ማግስት ጀመሮ ተቋማቱ ወደስራ መመለሳቸው ከሁለንተናዊ ችግር እንደታደጋቸው ያነሳሉ። በትራንስፖርት እየተንቀሳቀሱ፣ በኤሌክተሪክ ስራዎቻቸውን እየከወኑ ነው። ለሁለት ዓመታት የተቋረጠው አገልግሎት አቅርቦት እና የአገልግሎት ፈላጊዎች ፍላጎት ግን አሁንም ሙሉ በሙሉ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ የተጠቃሚዎችም፤ የአገልግሎት ሰጭዎችም ሀሳብ ነው። በሽሬ ስሁል ሆስፒታል የተመለከትኳቸው፤ ያነጋገርኳቸው፤ ከታዳጊዎች እስከ አዛውንት ዕድሜ ያሉ ህሙማን የሰላም አየር ማግኘታቸው የሕይወታቸው ዑደት እንዲቀጥል አድርጓል። ድንገተኛም ሆነ ነባር ህመም ያለባቸው ሰዎች በነጻ እየታከሙ ነው ያገኘኋቸው። ሰላም ከሌለ መታከም ቀርቶ በቅጡ ማስታመም፤ በወጉ መቀበርም እንደማይቻል ገልጸውልናል። የጤና፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት የግብዓት ክፍተቶች የማሟላት ሰራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም በፌዴራል ደረጃ በየተቋማቱ የተመደቡ አስተባባሪዎች አረጋግጠውልኛል። የጸጥታ አካሉና የህብረተሰቡ ትብብርም የሚያስቀና እንደሆነ ግለሰቦችም፤ የጸጥታ አካላትም ነግረውኛል። አክሱም ጺዮን ማርያም፣ ሽሬ ስላሴ ንግስ፣ የጥምቀት በዓላት ከሶስት ዓመታት በኋላ በአደባባይ ታቦት ወጥቶ ተከብሯል። የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮችም ይህንኑ ነው ያረጋገጡልኝ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት ቤተሰባዊ የሆኑ ይመስላል። እንቅስቃሴያቸውም የሰላማዊ ቀጠና መልክ ያለው ነው፤ ዩኒፎርም ከመልበሳቸው በስተቀር ጀሌያቸውን ይንቀሳቀሳሉ። ይህ ደግሞ መተማመን ከመፍጠር ባለፈ ጦርነት ውስጥ ለቆየ ማህበረሰብ ከስነ ልቦና ጫና እንዲላቀቅ አይነተኛ ሚና እንደላው ይሰማኛል። ኢ-መደበኛ የሽሬና አክሱም ወጎች ያረፍኩበት ሆቴል ባለቤት ‘አደይ’ ተግባቢ ናቸው። ደግ እናት ይመስላሉ። ከገባን ጀምሮ ‘ጠላ ተጎንጩ፤ ቡና ጠጡ’ ጭንቃቸው ነው። ሁለት ቀን ቡና አስፈልተውልናል፤ ጠላ አቅርበው ዘክረውናል። ይህ ሁሉ ሲሆንም ለከተማው እንግዳ መሆናችንን እንጂ ስለሙያችንም ሆነ ስለሌላ ማንነታችን አያውቁም ነበር። ብዙ መጨዋወትና ውሎ አዳር በኋላ ነው ጋዜጠኛ ስለመሆናችን ያወቁት። አደይ ተጨዋች ናቸው። አማርኛ ያዝ ቢያደርጋቸውም ጨዋታቸው ‘ኩርሽም’ ነው- ተሰምቶ የማይሰለች። በአጋጣሚ ‘ሰለክላካ’ ስለምትባለዋ ታሪካዊ ሥፍራ ጠይቄያቸው እያወጋን ነበር። ‘እንደእናንተ ወጣቶች ሳለን ‘ሰለክላካን ያላዬ ሸዋን ያመሰግናል’ ይባል ነበር። ታዲያ አንድ የሸዋ ሰው መጣና ሰለክላካን አየና ‘በቃ ይቺ ናት’ ሰለክላካ’ ብሎ ተገረመ” ብለው አሳቁን። (የፍቅር እስከ መቃብር መሪ ገጸ-ባህሪው ‘በዛብህ’ ወደ ዲማ ጊዮርጊስ ሄዶ ‘የዲማ መልኳ እና ዝናዋ’ ተጣርሶበት እንደተገረመበት ቅጽበት መሆኑ ነው)። አደይ የተጀመረው ሰላም ፍጹም ምሉዕ ሆኖ ወደ ቀደመ ኢትዮጵያዊ መልካችን የምንመለስበት ጊዜ እንዲመጣ ይሻሉ። ከጦር-ነት ወደ ሰላም-ነት! ቆንጂዬዋ ፊዮሪ የኮሌጅ ተማሪ ነበረች። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጀምሮ በኋላም በጦርነት ሳቢያ ትምህርቷን ካቆመች ሦስት ዓመታት ሆኗታል። ጦርነቱ ከቆመ በኋላ የጀበና ቡና ጀምራለች። ደንበኞቿ ሰብሰብ ብለን እንቀመጣለን። ፊዮሪ ከስኒ ማቅረቢያዋ ላይ አነስተኛ ጀበናዋን፤ የሚያማምሩ ስኒዎቿን እና መዓዛው ከሚያውድ የዕጣን ማጨሻዋ ጋር ሰድራ ይዛ ትቀርባለች። ከመካከላችን ካለው ጠረጴዛ ላይ ታስቀምጥና እርሷም ወንበር ይዛ ከመካከላችን ትቀመጣለች። ቡናው እስኪሰክን ጨዋታዋን ታስኮመኩመናለች። ቡናው ከሰከነ በኋላ ቡናዋን ቀድታ ለእያንዳንዳችን በእጃችን እያነሳች ትሰጣለች። በሽሬ ቡና የሚቀርበው በዚህ መልክ ነው። ለፊዮሪ እና መሰሎቿ ጦርነቱ ክፉ ጠባሳ መጣሉ፤ ተስፋቸው ላይ መጥፎ አሻራ ማስቀመጡን ታነሳለች። አሁን ግን ብሩህ ተስፋ ሰንቃለች። ስለነገዋም “ሰላሙ ይዝለቅልን፤ ትምህርቴን ለመቀጠል እመኛለሁ” ትላለች። አክሱም ከሽሬ በስተሰሜን 60 ኪሎ ሜትር ይርቃል። ከሽሬ አክሱም ስንንቀሳቀስ ከጥምቀት ዕለት በስተቀር ገበሬው የግብርና ሥራዎቹን እየከወነ ነበር። አርሶ አደሩ ያርሳል፤ መስኖውን ያለማል። የተዘራውን ውሃ ያጠጣል። የበቀለ ቡቃያውን ይኮተኩታል። ከጦርነት ወደ ልማት መዞሩን ዐይኔ ታዝቧል። በጥምቀት ዋዜማ፤ የከተራ በዓል ዕለት ሁለት ጎራማይሌ የረፋድ ትዕይንቶችን ላንሳ። ከአክሱም ከተማ ወደ አድዋ እና ሽሬ መገንጠያ አካባቢ ሰፊ የቀንድ ከብት ገበያ ነበር። እውነተኛ የዓመት በዓል ገበያ መልክ ያለው ትዕይንት ነበር። በተለይም የፍየል ዋጋ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተገበያዩ እንደነበር ሰምቻለሁ። ታሪካዊቷን አክሱም ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ የረገጥኳት/የተሳለምኳት ከአራት ዓመት በፊት በ2011 ዓ.ም ይመስለኛል። ከገበያው ቀጥሎ በታቦተ-ጽዮን መገኛዋ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ደጅ፣ በጥንታዊያኑ የአክሱም ሐውልት መገኛ አደባባይ ነበር። ከጽዮን በስተምዕራብ በአርባቱ እንሰሳ በኩል፤ በቅዱስ ያሬድ ዋርካ… አድርጌ በጽዮን ዋናው በር ደረስኩ። ማራኪ የአክሱም የኮብልስቶን መንገዶች ኦና ናቸው። የወትሮው ግርግር ናፍቋቸዋል። ከጽዮን ቅጥር ግቢ በዋናው በር በስተውጭ አነስተኛ እና ብቸኛ ዋንዛ በኮብልስቶን መሃል ነበረች። ዛሬም ለምልማ አለች። በዚህ አካባቢ ድሮ የነጭ ጎብኚ ጋጋታ፣ የጽዮን ደጅ ጠኚ ምዕመን… የተጨናነቀ ነበር። እንደ ድሮው የፎቶ አንሺ ግርግር፣ የአክሱም መስቀል ቀርጸው የሚሸጡ ወጣቶች ጫጫታ የለም። ይልቁንም እርጥባን የሚሹ አቅመ ደካሞችና ህፃናት ነበሩ። ጦርነት የሥፍራዋን መልክ አጠይሞታል። ያም ሆኖ ከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በኩሉሄ ባይባልም ወደነበረበት እየተመለሰ ነው። የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኰች ሥራ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከአክሱም ሐውልት ወደ ሌላ ሰፈር አቀናሁ። ትርሐስ ገና ታዳጊ ልጅ ነች። ጠይም፤ ስርጉድ፣ ሳቂታና ተረበኛ አይነት ልጅ ነች። እንደ ሽሬዋ ፊዮሪ መንገድ ዳር የጀበና ቡና እየሰራች ነው። ከሩቅ የመጣን እንግዶች መሆናችንን ስታውቅ፤ ደስታዋ ከገጿ ይነበብ ነበር። ያለፉ ጊዜያትን ሰቆቃ አጫወተችን። ስለቀጣይ ዕጣ ፈንታዋ እና ዕቅዷ ስታወራ ትቆይና “የሰው ልጅ ግን በጣም ከሃዲ ነው። ከወራት በፊትኮ ስለቢዝነስ አላስብም ነበር። መቼ እሞታለሁ እንጂ” ብላ ራሷን ትወቅሳለች። ወደ ሰማይ አንጋጣ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች። ጦርነት ተራውንም ሕዝብ ለመልከ-ብዙ ቀውስ ዳርጎት እንደቆየ ታነሳለች። ዛሬ ሁሉ አልፎ ሰላም መውረዱ ለመጨዋወት መብቃቷ ለእርሷ ትልቅ ብሥራት ነው። ይህ ለትርሐስ ብቻ ሳይሆን ለመላው አክሱማዊያን መሆኑ እሙን ነው። አክሱም ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በከተማዋ በሻለቃ አዛዥነት የተሰማራ የፌደራል ፖሊስ አባልም ያጋጠመውን አሳዛኝ ገጠመኞች አጫውቶኛል። ጦርነቱ ቢራዘም ኖሮ በተራው ሕዝብ ላይ ምን ያህል የከፋ ጉዳት ይደርስ እንደነበር በአሳዛኝ ሁኔታ ገልጾልኛል። አክሱሞች ያን ሁሉ አልፈው ሰላም አየር ነፍሶ፣ ከስጋት ቆፈን ተላቀው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሰዋል። የዛሬ ሳምንት ሰርክ(11 ሰዓት) ላይ አክሱም የከተራ በዓል በድምቀት አክብራለች። ታቦተ-ጽዮን ወደ ባህረ- ጥምቀቱ ስትወርድ፤ ወግና ሥርዓቱ ተጠብቆ፣ ሕዝቡ በሀበሻ ነጫጭ አልባሳት፣ ካህናት በልብሰ ተክህኖ ደምቀው … እየተከወነ ነበር። አንዲት እናት ለአማርኛ ተናጋሪ በቀረበ አነጋገር እያለቀሱ ታቦት እየሸኙ ነው። ትኩር ብዬ ሳያቸውም ዕንባቸው ዱብ ዱብ ይላል። “ከዚያ ሁሉ መከራ አልፎ ለዚህ በቃን፤ ተመስገን” እያሉ እልልታውን ያቀልጡታል። በደስታ እያነቡ ነበር። ይህ ስሜት የብዙኃኑ አክሱማዊያን እናቶች እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። አክሱም በኮቪድ እና በኋላም በጦርነቱ ምክንያት ባህረ-ምቀት ታቦት ወጥቶ ሲከበር ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ከወትሮው በተለየ ድምቀትና ውበት በሰላምና በደስታ፤ በአደባባይ እልልታና ሆታ በማክበራቸው ልዩ ስሜት ፈጥሮባቸዋልና! እናም በአክሱም የከተራ ሆነ የበዓለ-ጥምቀት ክብረ-በዓላት በሰላም ስምምነቱ ማግስት በድምቀት ተከውኖ አለፈ። የሃይማኖት አባቶቹም ሆኑ ምዕመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅም የዘንድሮው ክብረ-በዓል ካለፉት ዓመታት ነባራዊ ሁኔታ ጋር እያነጻጸሩ፤ ትልቅ ብሥራትና መልክ እንዳለው ገልጸዋል። ሰላም እንዲጸና፤ ነባር ኢትዮጵያዊ አንድነትና መተባበር እንዲመለስ ጽኑ መሻታቸውን ነግረውናል። በበጎ ቀን የማውቃትን አክሱም፤ ከረዥም ጊዜ በኋላ አሁናዊ መልኳን ታዝቤ፤ የነገ ትዝታ ሰንቄ ተመለስኩ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም