ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ፍጻሜን የስፔን እና የብራዚል አትሌቶች አሸነፉ
Sep 20, 2025 36
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2018 (ኢዜአ)፦ በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ፍጻሜን የስፔን እና የብራዚል አትሌቶች አሸንፈዋል። በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ፍጻሜ የስፔኗ አትሌት ማሪያ ፔሬዝ አሸንፋለች። አትሌቷ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 1 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ ፈጅቶባታል። ማሪያ እ.አ.አ በ2019 በሀንጋሪ ቡዳፔስት በተካሄደው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በተመሳሳይ ርቀት አሸናፊ እንደነበረች የሚታወስ ነው። አትሌቷ የቡዳፔስት ወርቋን በቶኪዮ ደግማለች። የሜክሲኮዋ አትሌት አሌና ጎንዛሌዝ 1 ሰዓት ከ26 ደቂቃ ከ06 ሴኮንድ፣ ጃፓናዊቷ አትሌት ናናኮ ፉጂ 1 ሰዓት ከ26 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል። ኢትዮጵያን ወክላ የተወዳደረችው ስንታየሁ ማስሬ አምስት ኪሎ ሜትር ላይ ውድድሩን አቋርጣለች። በተመሳሳይ የወንዶች የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ፍጻሜ የብራዚሉ ካዮ ቦንፊ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ አሸንፏል። በወንዶች ቻይናዊው ዣኦዣኦ ዋንግ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ43 ሴኮንድ ሁለተኛ፣ ስፔናዊው ፖል ማክግራዝ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ45 ሴኮንድ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ኢትዮጵያን ወክሎ የተወዳደረው ምስጋና ዋቁማ 1 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ17 ሴኮንድ 18ኛ ወጥቷል። ከሌሊቱ 9 ሰዓት ከ55 ላይ በተካሄደው የወንዶች የ20 ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር ፍጻሜ ፍጻሜ የብራዚሉ ካዮ ቦንፊም 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ አንደኛ ወጥቷል። ቻይናዊው ዣኦዣኦ ዋንግ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ43 ሴኮንድ ሁለተኛ፣ ስፔናዊው ፖል ማክግራዝ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ45 ሴኮንድ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ኢትዮጵያን ወክሎ የተወዳደረው ምስጋና ዋቁማ 1 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ17 ሴኮንድ 18ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል።
የጣና ሐይቅ ገዳማትና አዋሳኝ ውኃ አዘል መልከዓ-ምድርን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ ነው
Sep 19, 2025 104
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፡- የጣና ሐይቅ ደሴተ ገዳማትና አዋሳኝ ውኃ አዘል መልከዓ-ምድር የባህልና የተፈጥሮ መካነ-ቅርስ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን የቅርስ አሥተዳደር ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ፀሐይ እሸቴ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ቅርሱ በፈረንጆቹ ሐምሌ 2026 ዓ.ም በኮሪያ ሪፐብሊክ ቡሳን ከተማ በሚካሄደው የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ኮሚቴ 48ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ እንደሚመዘገብ ይጠበቃል። ለቅርሱ ምዝገባ አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎች አካል የሆነው የምዝገባ ሠነድ ቀደም ሲል ለዩኔስኮ ተልኮ ተቀባይነት ማግኘቱንም አስታውሰዋል። እንዲመዘገብ ከተጠየቀው ቅርስ ጋር በተያያዘ ሠነዱ ለጉባዔው ከመቅረቡ በፊት መከናወን ያለባቸው አስገዳጅ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በቀረበው የምዝገባ ሠነድ መሠረት የቅርሱን ይዘት እና ቅርሱ የሚገኝበትን ሁኔታ ለመገምገም በቅርቡ የዩኔስኮ ልዑክ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣም ጠቁመዋል። የልዑካን ቡድኑ አባላት ከዓለም አቀፍ የመታሰቢያ ሐውልቶች እና ስፍራዎች ምክር ቤት እና ከዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ቅርስ ጥበቃ ኅብረት የተውጣጡ ከፍተኛ የዘርፉ ምሁራን መሆናቸውን አመላክተዋል። እስካሁን ኢትዮጵያ 12 የሚዳሰሱ ቅርሶችን በዓለም አቀፍ ቅርስነት ማስመዝገቧንም አውስተዋል።
ኢትዮ-ሰርት ከአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅና የሙስሊም ትብብር ድርጅት አባል ሀገራት መካከል በተካሄደ የሳይበር መከላከልና ማጥቃት አቅም አሽናፊ ሆነ
Sep 19, 2025 94
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ):- በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የሳይበር አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ ማዕከል ከአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እንዲሁም ከሙስሊም ትብብር ድርጅት አባል ሀገራት ከተሳተፉበት የሳይበር መከላከልና ማጥቃት ውድድር አሸናፊ መሆኑ ተገለጸ። ኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ለኢዜአ በላከው መግለጫ ለአምስት ቀናት በሞሮኮ ራባት በተከናወነው የሳይበር ደህንነት ሳምንትን ተያይዞ በተከናወነ ውድድር ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ የሳይበር መከላከል ላይ የሚሰሩ ተቋማት ተሳትፈዋል። በተከናወነው ውድድር ከ30 በላይ ከሙስሊም ትብብር ድርጅት፣ ከአፍሪካና ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የተውጣጡ የሳይበር መከላከል ማዕከላት መሳተፋቸውም ተገልጿል። ተቋማቱ ባደረጉት የሳይበር መከላከልና ማጥቃት ውድድር የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ኢትዮጵያን በመወከል በአንደኝነት ማጠናቀቁን ጠቅሷል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር በሳይበር አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ ማዕከል አማካኝነት የሀገራችንን የዲጂታል ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ 24/7 በተጠንቀቅ የሚሰራና የሀገራችንን የሳይበር ምህዳር የሚጠብቅ ተቋም ነው። የተገኘው ውጤትም ለቀጣይ ስራዎች መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑን አስታውቋል። ከኢትዮጵያ በመቀጠል የካዛኪስታን የሳይበር አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ ማዕከል፣ የፓኪስታን ብሔራዊ የሳይበር ወንጀል ምርመራ ኤጀንሲ፣ ኤል ዋይ እንዲሁም የግብጽ የፋይናንሺያል የሳይበር ክስተት ምላሽ ቡድን ከሁለተኛ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ማጠናቀቃቸውም ተጠቅሷል።
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ይካሄዳሉ
Sep 19, 2025 89
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፦ በጃፓን ቶኪዮ እየተካሄደ የሚገኘው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ይደረጋሉ። ከሌሊቱ 7 ሰዓት ከ30 በሴቶች የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር አትሌት ስንታየሁ ማስሬ ትወዳደራለች። አትሌት ስንታየሁ በውድድሩ ላይ እንድትሳተፍ የተመረጠችው እ.አ.አ በ2024 በካሜሮን ዱዋላ በተካሄደው 23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በርቀቱ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘቷን ተከትሎ ነው። ስንታየሁ በካሜሮኑ ውድድር 1 ሰዓት ከ37 ደቂቃ ከ46 ሴኮንድ አንደኛ በመውጣት በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቷን ማስመዝገቧ የሚታወስ ነው። አትሌቷ እ.አ.አ በ2023 በጋና በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ጨዋታዎች በ20 ኪሎ ሜትር ርምጃ ተወዳድራ የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። እ.አ.አ በ2011 በኮትዲቭዋር አቢጃን በተደረገው ራተኛው ከ18 እና 20 ዓመት በታች የአፍሪካ ታዳጊዎች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ10 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ሶስተኛ በመውጣት የነሐስ ሜዳሊያ ማግኘቷ የሚታወስ ነው። በተጨማሪም ስንታየሁ እ.አ.አ በ2018 በአልጄሪያ በተካሄደው ሶስተኛ የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታ በአምስት ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። ከሌሊቱ 9 ሰዓት ከ55 በሚደረገው የወንዶች የ20 ኪሎ ሜትር ርምጃ ፍጻሜ አትሌት ምስጋና ዋቁማ ኢትዮጵያን ወክሎ ይወዳደራል። አትሌት ምስጋና በውድድሩ ላይ እንዲሳተፍ የተመረጠው በ20 ኪሎ ሜትር የወንዶች ርምጃ ዓለም አቀፍ የደረጃ ሰንጠረዥ 14ኛ ላይ በመገኘቱ ባገኘው የተሳትፎ ኮታ ነው። ምስጋና እ.አ.አ በ2024 በፓሪስ በተካሄደው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች በ20 ኪሎ ሜትር የወንዶች ርምጃ ውድድር ስድስተኛ መውጣቱ ይታወሳል። በወቅቱ 1 ሰዓት ከ19 ደቂቃ ከ31 ሴኮንድ የገባበት ጊዜ የርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቱ ነው። አትሌቱ እ.አ.አ በተርኪዬ አንታሊያ በተካሄደው የዓለም የርምጃ ውድድር ሻምፒዮና 1 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ51 ሴኮንድ 10ኛ ወጥቷል። እ.አ.አ በ2023 በጋና በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ጨዋታዎች እና እ.አ.አ በ2024 በካሜሮን ዱዋላ በተካሄደው 23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በርቀቱ የወርቅ ሜዳሊያዎችን አግኝቷል። በርምጃ ውድድሮች ስንታየሁ ማስሬ እና ምስጋና ዋቁማ ጠንካራ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
በጠንካራ አንድነት ያሳካነውን ግዙፍ ፕሮጀክት በሌሎች ዘርፎች ላይም ለመድገም ቁርጠኞች ነን-የህዝባዊ ሰልፍ ታዳሚዎች
Sep 19, 2025 130
ቦንጋ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ) :- በጠንካራ አንድነት ያሳካነውን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሌሎች የልማት ዘርፎች ለመድገም ቁርጠኛ ነን ሲሉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቦንጋ ከተማ የህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ታዳሚዎች ገለፁ። የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ክልል አቀፍ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በቦንጋ ከተማ ተካሄዷል። የሰልፉ ታዳሚዎች ፤ በጠንካራ አንድነት ያሳካነውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሌሎች የልማት ዘርፎች ለመድገም ቁርጠኛ ነን ሲሉ ገልጸዋል። በክልሉ ከቤንች ሸኮ ዞን የመጡት አቶ ወልደየስ ዘለቀ እና ከሸካ ዞን የመጡት ኢንስፔክተር ደመረ አገሎ የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ አንድ ከሆንን የማንወጣው ነገር እንደሌለ ማሳያ ነው ብለዋል። የትውልዱ ኩራትና ዳግማዊ አድዋ የሆነውን የህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማጠናቀቅ ያሳየነውን ድጋፍና ህብረት በሌሎች ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ስራዎች ላይ ለመድገም ቁርጠኛ ነን ብለዋል። ዳግማዊ አድዋ በዘመናችን ተፈፅሞ በማየታችን ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል ያሉት የቦንጋ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ሀና ወልደማሪያም እና ከኮንታ ዞን የመጡት ሻምበል ጀበሌ ዱላ ናቸው። በቀጣይም ኢትዮጵያ የሰነቀችው ራዕይ ተሳክቶ ለማየት እንደሀገር የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል። በህዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ "የህዳሴው ግድብ የህብረታችን አርማ የብልፅግናችን አሻራ ነው" ብለዋል። በጋራ መቆማችን ውስብስብ ችግሮችን ተሻግረን ትልልቅ የልማት ውጥኖችን ማሳካት እንደሚቻል ያረጋገጠ ነው ያሉት ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ከተባበርንና በጋራ ከቆምን ከከፍታ ጉዟችን የሚያስቆመን ኃይል የለም ሲሉም ተናግረዋል። ግድቡ በላባችን፣ በደማችንና በገንዘባችን ያፀናነው ሕያው የምህንድስና ጥበብና የማህበረሰብ የወል ቅርስ ነው በማለት ይህን ግዙፍ ፕሮጀክት በማጠናቀቅ ያሳየነውን ስኬት በሌሎች ላይም እንደግማለን ሲሉ አረጋግጠዋል። በቦንጋ ከተማ በተካሄደው ክልል አቀፍ የደስታ መግለጫ ሰልፍ ላይ የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ ከሁሉም ዞኖች የተወጣጡ የህብረተሰብ ተወካዮችና የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ጋር ተወያዩ
Sep 17, 2025 456
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ጋር መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልእክት "ዛሬ በአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አማካሪ የሆኑትን ማሳድ ቡሎስን በጽሕፈት ቤታችን አግኝቼ ሰፊ አድማስ ባላቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል" ሲሉ ገልጸዋል።
የመደመር መንግሥት ማደግ ለሚፈልጉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ ነው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 302
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የመደመር መንግሥት መጽሐፍ፤ ጊዜ ተሰጥቶናል በግልጽ ምልከታና እሳቤ ሀገራችንን ብንሠራ ታሪክ ሠሪዎች እንጂ ዘካሪዎች አንሆንም በሚል የተዘጋጀ ሠነድ ነው ብለዋል። ይህም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት ማጠንጠኛው “አራት መ” መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የመጀመሪያው “መ” መነሻ ነው ብለዋል። መነሻውም ቁጭት መሆኑን ነው ያስረዱት። ኢትዮጵያ ለምን ድሃ ሆነች? ኢትዮጵያ ለምን ተረጂ ሆነች? ኢትዮጵያ ከማን ስለምታንስ ነው ከማን የምትረዳው? የሚሉ የቁጭት ጥያቄዎች እና ምክንያት ፍለጋ ነው መነሻው ብለዋል። አሳማኝ ምክንያት ካልተገኘለት ቁጭት ያንገበግባል፤ እንቅልፍ ይነሳል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ለመደመር መንግሥት መነሻ ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ምንም እንኳን በርካታ ድሃ ሀገራት ቢኖሩም የኢትዮጵያ ድሃ መሆን የሚያንገበግበው ግን፤ ምድረ ቀደምት መሆኗ፣ የነጻነት ገድል ያላት፣ በባህልና በታሪክ የሚያኮራ ሥራ ያላት በመሆኗ ነው ብለዋል። እንደ ምድረ ቀደምትነት የግብርና ሥራን ቀድመን ብንጀምርም፤ እስካሁን አሠራራችን በሚፈለገው ልክ በቴክኖሎጂ አለማደጉ ይቆጫል። በሽመና እንዲሁም በባህል መድኃኒት ነባር ልምድ ያለን ሀገር እንዴት በስፋት ማምረት እና ራሳችንን መቻል ተሳነን? የሚል ቁጭት መነሻ መሆኑንም አስረድተዋል። ከቁጭት በተጨማሪ መንፈሳዊ ቅናት ለመደመር መንግሥት መነሻ እንደሆነም አብራርተዋል። የመደመር መንግሥት ከተገነዘባቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል፤ የተዛቡ ጥያቄዎች መኖር እና ለዚህም ደግሞ አፍራሽ የለውጥ ሂደት መከተል የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል። የሕዳሴ ግድብ አንድ መንግሥትና ግለሰብ ስኬት ሳይሆን፤ የመላ ኢትዮጵያውን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ገድል መሆኑንም አስረድተዋል።
የእኛ መሻት የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 306
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የእኛ መሻት የምትመስል ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ የመደመር መንግሥት ውጤት ከሰማነው፣ ካነበብነው ብቻ ሳይሆን በተግባር ስንሞክር ካየነው ውጣ ውረድ ጭምር የተቀዳ ነው ብለዋል። በዚህም ብዙዎች የሚማሩበት፣ የሚያሳድጉት፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የሚተጉበት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም ነው ያሉት። የመፈጸም ብቃታችንን በብዙ መንገድ ዐይተናል፤ የእኛ መሻት የምትመስል ሀገር ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። ብዙ ጊዜ ለመምሰል ሞክረን አልተሳካም፤ አሁን በእኛ መልክ፣ በእኛ እሳቤ፣ በእኛ ባህል ልክ ተቀርጾ በምሳሌነት የሚወሰድ ሀገር መገንባት እንፈልጋለን ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እንደሚቻልም የመደመር መንግሥት በጽኑ ያምናል ሲሉ አስረድተዋል። ለአብነትም የአረንጓዴ ዐሻራን ሥራ ጠቅሰው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ 48 ቢሊየን ችግኝ መትከል በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ማንም ያልሞከረው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የምንመሰልበት ሆኖ በታሪክ ማኅደር ይቀመጣል ነው ያሉት በንግግራቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም በትጋትና በቅንጅት ያሰብነውን ማሳካት እንደምንችል ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።
የምንደመረው ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 350
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች ብለዋል። ለሀገራዊ ዕድገታችን ሁነኛው መንገድ መተባበር እና መደመር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ በምሳሌነት እንድትጠቀስ የሚያስችሉ በርካታ ራዕዮቻችንን ለማሳካት መነሻ ከያዝን፣ መዳረሻ ከአበጀን በኋላ እንዴት ባለ መንገድ መፈጸም አለብን የሚለው ትልቅ ጉዳይ መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህ ደግሞ በእንዴት ያለ መንገድ እንሂድ የሚለው በመደመር መንግሥት መመላከቱን አንስተዋል። በዚህም መሠረት ራዕዮቻችንን ለማሳካት ከሚረዱ መንገዶች መካከል አንዱ ከውስጥ ወደ ውጭ መመልከት ነው ብለዋል። በየዘርፉ የካበተ ዕውቀት ያላት ኢትዮጵያ ለማስተማር እንጂ ከሌሎች ለመማር የምትጓጓ መሆን እንደሌለባትም ጠቅሰዋል። ያለፉን፣ የቀደሙን፣ የሰለጠኑ፣ የፈጠሩ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህ የሚበጀንን መቅዳት ሳይሆን መማር ይጠቅማል ብለዋል። ከሌሎች ሀገራት ስንማርም የእኛን መርምረንና አሰናስለን ግልጽ ሐሳብ መያዝ ስንችል፤ የአቅምና አቋም ድምር ስንፈጥር መሆን አለበት ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ውስጥ የአቅም እና አቋም ድምር ከፈጠርን ተዓምር መሥራት እንችላለን ሲሉም ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር)
Sep 17, 2025 332
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግርም፤ የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያውያንን በጋራ ራዕይ ላይ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ብለዋል። ኢትዮጵያውያን በጋራ ራዕይ ላይ ከተሰባሰቡ በኋላ፤ ስብራት ለይተን መፍትሔ ማበጀት ያስፈልጋል ሲሉም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የእድገት ጉዞ እና የፖለቲካ ችግር ስብራት የጠላቶቻችን አጀንዳ የሆነው መለያየት ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህ መፈወሻ መድኃኒቱ ደግሞ መደመር ብቻ ነው ሲሉ አስረድተዋል። በጋራ መቆም ብንችል መፍጠን እንችላለን፤ መፍጠር እንችላለን፤ በአስፈላጊው ቦታ ደግሞ መከተል ሳይሆን መዝለል እንችላለን ነው ያሉት። አክለውም በጋራ ስንቆም ከተቀባይነትና ተከታይነት መላቀቅ እንችላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሐሳብ ተቀብለን፣ ገንዘብ ተቀብለን፣ ተልዕኮ ተቀብለን ኢትዮጵያ ላይ መለማመድ ተገቢ አይደለም በማለት በአጽንኦት ገልጸዋል። በሥነ-ልቦና ስብራት መኖሩንና ጥሩ ነገሮች ሲታዩ የኢትዮጵያ እንደሆነ ያለመቀበል ተገቢነት የሌለው ልምምድ መኖሩንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እንደምትችል እና በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኗን መቀበል እንደሚገባም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መክረዋል።
የመደመር መንግሥት ከትናንት እስረኝነት የተላቀቀና ለምክንያታዊነት ትኩረት የሰጠ ነው
Sep 17, 2025 321
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት ከትናንት እስረኝነት የተላቀቀና ለምክንያታዊነት ትኩረት የሰጠ መሆኑን በመደመር መንግሥት መጽሃፍ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀረቡ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በመደመር እሳቤ የጻፉት 4ኛው መጽሃፍ ''የመደመር መንግሥት'' ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። በመጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመጽሃፉ ደራሲና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል። በመጽሃፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር ዳኛቸው አሰፋ(ዶ/ር)፣ መጽሃፉ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ችግሮች ላይ ንደፈ ሃሳባዊ ትንተና ብቻ ሳይሆን ተግባራዊ ምላሽ የሚያመላክት መሆኑንም አብራርተዋል። ለችግሮች አውዱን የተገነዘበ ሙሉ መፍትሄ ማስቀመጥ እንደሚገባ በመጽሃፉ በግልጽ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ይህም አንድ መንገድን ብቻ ከሚከተል የርዕዮት እስረኝነት የተላቀቀ አካሄድ ነው ብለዋል። መጽሃፉ የያዛቸው ትንተናዎች በምክንያታዊነት ላይ ያረፉና ለምክንያታዊነት ክፍት መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል። መጽሃፉ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የት እንዳለችና መጻኢ ጉዞዋ ምን መምሰል እንዳለበትም በግልጽ ያስቀምጣል ነው ያሉት። በተጨማሪም በዜጎች መካከል መተባበርና መደጋገፍ እንዲኖር መንገድ በማሳየት ሰላምና አብሮነት እንዲጎለብት ዝርዝር ሃሳብ ማስቅመጡንም አንስተዋል። ሌላኛው በመጽሃፉ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀረቡት የፖለቲካ ተንታኙ ዘሪሁን ተሾመ በበኩላቸው፤ መጽሃፉ ትናትን በልኩ የሚገነዘብና በትናንት እሳቤ ላይ ያልቆመ ስለመሆኑ አብራርተዋል። የዛሬ ችግሮችን በተገቢው መንገድ እንደሚዳስስ ጠቅሰው፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች የተሻለ ነገን ከመገንባት የሚያስቆሙ እንዳልሆኑ በግልጽ እንደሚያመላክትም ነው ያነሱት። በመጽሃፉ የተዳሰሱ ሃሳቦችም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ የሚበጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
የመደመር መንግስት መጽሃፍ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰና መፍትሄ ያመላከተ ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Sep 17, 2025 366
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግስት መጽሃፍ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰና መፍትሄ ያመላከተ ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጻፈው የመደመር መንግስት መጽሃፍ ዛሬ ለንባብ በቅቷል። በመጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ፕሬዝዳነት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመጽሃፉ ደራሲና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል። በመጽሐፍ ላይ ዳሰሳ ካቀረቡት መካከል የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ እንዳሉት፣ መጽሃፉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሁኔታ የሚያስቃኝ ነው። በተለይ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰ እና ተግባራዊ መፍትሄዎችን ያመላከተ መሆኑንም ተናግረዋል። መጽሃፍ አስተሳሰብ ላይ ትኩረት አድርጎ ከቁጭት እንደሚነሳ ጠቅሰው፣ ይህም ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ነው ያብራሩት። መጽሃፉ ነገሮችን አፍርሶ ከመስራት ይልቅ አዎንታዊውን ማስቀጠል፣ አሉታዊውን ደግሞ ማስተካከልን እንደሚያመላክትም አንስተዋል። ይህም ኢትዮጵያ ለዘመናት የሄደችበትን ተቸካይ የፖለቲካ አካሄድ የቀየረ አተያይ ስለመሆኑም አብራርተዋል። መጽሃፉ ፖለቲካችን ያሸነፈ አካል እንደፈለገ ሁሉን ይጠቅልል ከሚል አካሄድ የሚያወጣ ነው ብለዋል። ''እኔ የፈለኩት ካልሆነ'' ከሚል የዜሮ ድምር ጨዋታ መውጣት የሚቻልበትን ዘመናዊ የፖለቲካ አካሄድ ያመላከተ ስለመሆኑም አቶ ጌታቸው አብራርተዋል። በሌላ በኩል ዜጎች ከመሰረታዊ ፍላጎት ባሻገር በክብር የመኖር ህልማቸውን ለመመለስ አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ችግሮች በነበረው አካሄድ ትርጉም ባለው መልኩ መፍታት እንደማይቻል አንስተው፣ የመደመር እሳቤ ተግባራዊ ያደረገው መፍጠርና መፍጠን በዚህ ረገድ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማን የተከማቸ ችግር ለመፍታት የተተገበረው የመፍጠርና መፍጠን መፍትሄ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ መሆኑንም ተናግረዋል። አዲስ አበባን ለመለወጥ የተጀመረው ስራ አዲስ የስራ ባህልን ያለማመደ መሆኑንም ገልጸዋል። በቀጣይ በአዲስ አበባ የታየው አዲስ ተስፋ ወደ ሁሉም የኢትዮጵያ አቅጣጫ እንዲሰፋ መረባረብ ይገባል ነው ያሉት። መጽሃፉ ለማንበብ ምቹ በሆነ አቀራረብ መዘጋጀቱን የተናገሩት አቶ ጌታቸው፣ ሁሉም እንዲያነበውም ጥሪ አቅርበዋል።
ፖለቲካ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ጋር ተወያዩ
Sep 17, 2025 456
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ጋር መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልእክት "ዛሬ በአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አማካሪ የሆኑትን ማሳድ ቡሎስን በጽሕፈት ቤታችን አግኝቼ ሰፊ አድማስ ባላቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል" ሲሉ ገልጸዋል።
የመደመር መንግሥት ማደግ ለሚፈልጉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ ነው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 302
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የመደመር መንግሥት መጽሐፍ፤ ጊዜ ተሰጥቶናል በግልጽ ምልከታና እሳቤ ሀገራችንን ብንሠራ ታሪክ ሠሪዎች እንጂ ዘካሪዎች አንሆንም በሚል የተዘጋጀ ሠነድ ነው ብለዋል። ይህም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት ማጠንጠኛው “አራት መ” መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የመጀመሪያው “መ” መነሻ ነው ብለዋል። መነሻውም ቁጭት መሆኑን ነው ያስረዱት። ኢትዮጵያ ለምን ድሃ ሆነች? ኢትዮጵያ ለምን ተረጂ ሆነች? ኢትዮጵያ ከማን ስለምታንስ ነው ከማን የምትረዳው? የሚሉ የቁጭት ጥያቄዎች እና ምክንያት ፍለጋ ነው መነሻው ብለዋል። አሳማኝ ምክንያት ካልተገኘለት ቁጭት ያንገበግባል፤ እንቅልፍ ይነሳል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ለመደመር መንግሥት መነሻ ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ምንም እንኳን በርካታ ድሃ ሀገራት ቢኖሩም የኢትዮጵያ ድሃ መሆን የሚያንገበግበው ግን፤ ምድረ ቀደምት መሆኗ፣ የነጻነት ገድል ያላት፣ በባህልና በታሪክ የሚያኮራ ሥራ ያላት በመሆኗ ነው ብለዋል። እንደ ምድረ ቀደምትነት የግብርና ሥራን ቀድመን ብንጀምርም፤ እስካሁን አሠራራችን በሚፈለገው ልክ በቴክኖሎጂ አለማደጉ ይቆጫል። በሽመና እንዲሁም በባህል መድኃኒት ነባር ልምድ ያለን ሀገር እንዴት በስፋት ማምረት እና ራሳችንን መቻል ተሳነን? የሚል ቁጭት መነሻ መሆኑንም አስረድተዋል። ከቁጭት በተጨማሪ መንፈሳዊ ቅናት ለመደመር መንግሥት መነሻ እንደሆነም አብራርተዋል። የመደመር መንግሥት ከተገነዘባቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል፤ የተዛቡ ጥያቄዎች መኖር እና ለዚህም ደግሞ አፍራሽ የለውጥ ሂደት መከተል የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል። የሕዳሴ ግድብ አንድ መንግሥትና ግለሰብ ስኬት ሳይሆን፤ የመላ ኢትዮጵያውን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ገድል መሆኑንም አስረድተዋል።
የእኛ መሻት የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 306
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የእኛ መሻት የምትመስል ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ የመደመር መንግሥት ውጤት ከሰማነው፣ ካነበብነው ብቻ ሳይሆን በተግባር ስንሞክር ካየነው ውጣ ውረድ ጭምር የተቀዳ ነው ብለዋል። በዚህም ብዙዎች የሚማሩበት፣ የሚያሳድጉት፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የሚተጉበት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም ነው ያሉት። የመፈጸም ብቃታችንን በብዙ መንገድ ዐይተናል፤ የእኛ መሻት የምትመስል ሀገር ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። ብዙ ጊዜ ለመምሰል ሞክረን አልተሳካም፤ አሁን በእኛ መልክ፣ በእኛ እሳቤ፣ በእኛ ባህል ልክ ተቀርጾ በምሳሌነት የሚወሰድ ሀገር መገንባት እንፈልጋለን ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እንደሚቻልም የመደመር መንግሥት በጽኑ ያምናል ሲሉ አስረድተዋል። ለአብነትም የአረንጓዴ ዐሻራን ሥራ ጠቅሰው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ 48 ቢሊየን ችግኝ መትከል በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ማንም ያልሞከረው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የምንመሰልበት ሆኖ በታሪክ ማኅደር ይቀመጣል ነው ያሉት በንግግራቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም በትጋትና በቅንጅት ያሰብነውን ማሳካት እንደምንችል ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።
የምንደመረው ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 350
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች ብለዋል። ለሀገራዊ ዕድገታችን ሁነኛው መንገድ መተባበር እና መደመር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ በምሳሌነት እንድትጠቀስ የሚያስችሉ በርካታ ራዕዮቻችንን ለማሳካት መነሻ ከያዝን፣ መዳረሻ ከአበጀን በኋላ እንዴት ባለ መንገድ መፈጸም አለብን የሚለው ትልቅ ጉዳይ መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህ ደግሞ በእንዴት ያለ መንገድ እንሂድ የሚለው በመደመር መንግሥት መመላከቱን አንስተዋል። በዚህም መሠረት ራዕዮቻችንን ለማሳካት ከሚረዱ መንገዶች መካከል አንዱ ከውስጥ ወደ ውጭ መመልከት ነው ብለዋል። በየዘርፉ የካበተ ዕውቀት ያላት ኢትዮጵያ ለማስተማር እንጂ ከሌሎች ለመማር የምትጓጓ መሆን እንደሌለባትም ጠቅሰዋል። ያለፉን፣ የቀደሙን፣ የሰለጠኑ፣ የፈጠሩ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህ የሚበጀንን መቅዳት ሳይሆን መማር ይጠቅማል ብለዋል። ከሌሎች ሀገራት ስንማርም የእኛን መርምረንና አሰናስለን ግልጽ ሐሳብ መያዝ ስንችል፤ የአቅምና አቋም ድምር ስንፈጥር መሆን አለበት ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ውስጥ የአቅም እና አቋም ድምር ከፈጠርን ተዓምር መሥራት እንችላለን ሲሉም ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር)
Sep 17, 2025 332
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግርም፤ የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያውያንን በጋራ ራዕይ ላይ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ብለዋል። ኢትዮጵያውያን በጋራ ራዕይ ላይ ከተሰባሰቡ በኋላ፤ ስብራት ለይተን መፍትሔ ማበጀት ያስፈልጋል ሲሉም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የእድገት ጉዞ እና የፖለቲካ ችግር ስብራት የጠላቶቻችን አጀንዳ የሆነው መለያየት ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህ መፈወሻ መድኃኒቱ ደግሞ መደመር ብቻ ነው ሲሉ አስረድተዋል። በጋራ መቆም ብንችል መፍጠን እንችላለን፤ መፍጠር እንችላለን፤ በአስፈላጊው ቦታ ደግሞ መከተል ሳይሆን መዝለል እንችላለን ነው ያሉት። አክለውም በጋራ ስንቆም ከተቀባይነትና ተከታይነት መላቀቅ እንችላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሐሳብ ተቀብለን፣ ገንዘብ ተቀብለን፣ ተልዕኮ ተቀብለን ኢትዮጵያ ላይ መለማመድ ተገቢ አይደለም በማለት በአጽንኦት ገልጸዋል። በሥነ-ልቦና ስብራት መኖሩንና ጥሩ ነገሮች ሲታዩ የኢትዮጵያ እንደሆነ ያለመቀበል ተገቢነት የሌለው ልምምድ መኖሩንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እንደምትችል እና በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኗን መቀበል እንደሚገባም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መክረዋል።
የመደመር መንግሥት ከትናንት እስረኝነት የተላቀቀና ለምክንያታዊነት ትኩረት የሰጠ ነው
Sep 17, 2025 321
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት ከትናንት እስረኝነት የተላቀቀና ለምክንያታዊነት ትኩረት የሰጠ መሆኑን በመደመር መንግሥት መጽሃፍ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀረቡ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በመደመር እሳቤ የጻፉት 4ኛው መጽሃፍ ''የመደመር መንግሥት'' ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። በመጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመጽሃፉ ደራሲና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል። በመጽሃፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር ዳኛቸው አሰፋ(ዶ/ር)፣ መጽሃፉ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ችግሮች ላይ ንደፈ ሃሳባዊ ትንተና ብቻ ሳይሆን ተግባራዊ ምላሽ የሚያመላክት መሆኑንም አብራርተዋል። ለችግሮች አውዱን የተገነዘበ ሙሉ መፍትሄ ማስቀመጥ እንደሚገባ በመጽሃፉ በግልጽ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ይህም አንድ መንገድን ብቻ ከሚከተል የርዕዮት እስረኝነት የተላቀቀ አካሄድ ነው ብለዋል። መጽሃፉ የያዛቸው ትንተናዎች በምክንያታዊነት ላይ ያረፉና ለምክንያታዊነት ክፍት መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል። መጽሃፉ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የት እንዳለችና መጻኢ ጉዞዋ ምን መምሰል እንዳለበትም በግልጽ ያስቀምጣል ነው ያሉት። በተጨማሪም በዜጎች መካከል መተባበርና መደጋገፍ እንዲኖር መንገድ በማሳየት ሰላምና አብሮነት እንዲጎለብት ዝርዝር ሃሳብ ማስቅመጡንም አንስተዋል። ሌላኛው በመጽሃፉ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀረቡት የፖለቲካ ተንታኙ ዘሪሁን ተሾመ በበኩላቸው፤ መጽሃፉ ትናትን በልኩ የሚገነዘብና በትናንት እሳቤ ላይ ያልቆመ ስለመሆኑ አብራርተዋል። የዛሬ ችግሮችን በተገቢው መንገድ እንደሚዳስስ ጠቅሰው፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች የተሻለ ነገን ከመገንባት የሚያስቆሙ እንዳልሆኑ በግልጽ እንደሚያመላክትም ነው ያነሱት። በመጽሃፉ የተዳሰሱ ሃሳቦችም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ የሚበጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
የመደመር መንግስት መጽሃፍ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰና መፍትሄ ያመላከተ ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Sep 17, 2025 366
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግስት መጽሃፍ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰና መፍትሄ ያመላከተ ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጻፈው የመደመር መንግስት መጽሃፍ ዛሬ ለንባብ በቅቷል። በመጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ፕሬዝዳነት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመጽሃፉ ደራሲና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል። በመጽሐፍ ላይ ዳሰሳ ካቀረቡት መካከል የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ እንዳሉት፣ መጽሃፉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሁኔታ የሚያስቃኝ ነው። በተለይ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰ እና ተግባራዊ መፍትሄዎችን ያመላከተ መሆኑንም ተናግረዋል። መጽሃፍ አስተሳሰብ ላይ ትኩረት አድርጎ ከቁጭት እንደሚነሳ ጠቅሰው፣ ይህም ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ነው ያብራሩት። መጽሃፉ ነገሮችን አፍርሶ ከመስራት ይልቅ አዎንታዊውን ማስቀጠል፣ አሉታዊውን ደግሞ ማስተካከልን እንደሚያመላክትም አንስተዋል። ይህም ኢትዮጵያ ለዘመናት የሄደችበትን ተቸካይ የፖለቲካ አካሄድ የቀየረ አተያይ ስለመሆኑም አብራርተዋል። መጽሃፉ ፖለቲካችን ያሸነፈ አካል እንደፈለገ ሁሉን ይጠቅልል ከሚል አካሄድ የሚያወጣ ነው ብለዋል። ''እኔ የፈለኩት ካልሆነ'' ከሚል የዜሮ ድምር ጨዋታ መውጣት የሚቻልበትን ዘመናዊ የፖለቲካ አካሄድ ያመላከተ ስለመሆኑም አቶ ጌታቸው አብራርተዋል። በሌላ በኩል ዜጎች ከመሰረታዊ ፍላጎት ባሻገር በክብር የመኖር ህልማቸውን ለመመለስ አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ችግሮች በነበረው አካሄድ ትርጉም ባለው መልኩ መፍታት እንደማይቻል አንስተው፣ የመደመር እሳቤ ተግባራዊ ያደረገው መፍጠርና መፍጠን በዚህ ረገድ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማን የተከማቸ ችግር ለመፍታት የተተገበረው የመፍጠርና መፍጠን መፍትሄ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ መሆኑንም ተናግረዋል። አዲስ አበባን ለመለወጥ የተጀመረው ስራ አዲስ የስራ ባህልን ያለማመደ መሆኑንም ገልጸዋል። በቀጣይ በአዲስ አበባ የታየው አዲስ ተስፋ ወደ ሁሉም የኢትዮጵያ አቅጣጫ እንዲሰፋ መረባረብ ይገባል ነው ያሉት። መጽሃፉ ለማንበብ ምቹ በሆነ አቀራረብ መዘጋጀቱን የተናገሩት አቶ ጌታቸው፣ ሁሉም እንዲያነበውም ጥሪ አቅርበዋል።
ማህበራዊ
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶቹ በመቀሌ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ አስጀመሩ
Sep 19, 2025 135
መቀሌ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፡- የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በመቀሌ ከተማ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ማስጀመሪያ የመሰረት ድንጋይ አኖሩ። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች እየተለመዱና እየተስፋፉ ሲሆን፤ በተለይም የአቅመ ደካማ ወገኖች እና አረጋውያንን ቤቶች በማደስና በመገንባት ጭምር በርካታ ተቋማትና ግለሰቦች እየተሳተፉ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጭምር የሚሳተፉበት የቤት ግንባታና እድሳት ተግባር እየተከናወነ ነው። በዚህም መሰረት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በመቀሌ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ማስጀመሪያ የመሰረት ድንጋይ አኑረዋል። የግንባታውን የመሰረት ድንጋይም የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ወሀብረቢ ሁለቱንም ተቋማት በመወከል አስቀምጠዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ሚኒስትሯ ባደረጉት ንግግር፤ የመኖሪያ ቤቶቹ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቀው ለነዋሪዎች ይተላለፋል ብለዋል። በመኖሪያ ቤት ግንባታውም ይሁን በሌሎች በጎ ተግባራት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸው በሁሉም አካባቢዎች ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። ከዚሁ መርሃ ግብር በተጓዳኝም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶቹ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል።
ሰውን በሕገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን ከመከላከል ጎን ለጎን ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ሊጠናከር ይገባል
Sep 19, 2025 142
አዳማ፤ መስከረም 9/2018(ኢዜአ)፦ሰውን በሕገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን ከመታገል ጎን ለጎን ቀላል፣ መደበኛና ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ሊጠናከር እንደሚገባ የፍትህ ሚኒስቴር አስገነዘበ። ሚኒስቴሩ በዓለም አቀፍ የፍልሰት ድርጅት እና በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት ድጋፍ የትብብር ጥምረቶች የ2017 የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ለመምከር ያዘጋጀው መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ እንዳሉት ዜጎች በተለያዩ ምክንያቶች ሀገራቸውን ለቀው ወደ ተለያዩ ሀገራት ይፈልሳሉ። በፍልሰቱም የመተላለፊያና የመዳረሻ ሀገራትን የፍልሰት ህጎችና አሠራሮች ባልተከተለና መደበኛ ባልሆነ መንገድ የህገወጥ መልማዮች፣ደላሎችና የተደራጁ የወንጀል ቡድኖች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። ይህም ዜጎችን ለሞት፣ ለጉልበት ብዝበዛ፣ ለእንግልትና ለከፋ ሰብአዊ መብት ጥሰቶች እየዳረጋቸው መሆኑን ጠቁመዋል። ለችግሩ ምላሽ ለመስጠት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ ሰውን በሕገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን ከመታገል ጎን ለጎን ቀላል፣ መደበኛና ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት መከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ህገ ወጥ ፍልሰትን ለመቀነስ ከሀገራዊ ኢኮኖሚ ሪፎርም ጋር አጣጥሞ ለማስኬድ የ10 አመት መሪ እቅድ መነደፉንም አክለዋል። በተለይ በሰው የመነገድና በሕገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን ለመከላከል ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ማጽደቅን ጨምሮ የትብብር አደረጃጀቶችን በመዘርጋት እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን አቶ በላይሁን አብራርተዋል። በፍትህ ሚኒስቴር የብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብርሃም አያሌው በበኩላቸው ባለፈው በጀት ዓመት በሰው የመነገድና ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በዚሁ ህግ የማስከበር ስራ 600 የሚጠጉ ግለሰቦች በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ተከሰው ከ10 እስከ 25 ዓመት የእስር ቅጣት እንደተፈረደባቸው ተናግረዋል። የስደት ተጎጂዎችን ጥበቃና መልሶ በማቋቋም ረገድም ከ90 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን ተናግረዋል። ባለፈው በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ፍልሰተኞችን ለመታደግም ለ504 ሺህ ዜጎች የውጭ አገር የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን አውስተዋል። በዓለም ዓቀፉ የህፃናት አድን ድርጅት በኢትዮጵያ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ኃይለየሱስ ፀሐይ፤ ድርጅቱ በህዝብ ላይ ችግር እየሆነ የመጣውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመታደግ መንግሥት የሚያደርገውን ሁለንተናዊ ጥረት እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ ህጻናት በፍልሰቱ እንደሚጠቁና ለችግር እንደሚጋለጡ ጠቁመው ህጻናቱን ከዚህ ችግር ለማላቀቅ የሚሰሩ ስራዎችን ከማጠናከርና ከመደገፍ አንፃር ፕሮግራሙ የክትትልና የአቅም ግንባታ ስራ በመስራት ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እያበቃ ነው
Sep 19, 2025 87
ጭሮ ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፦የኦሮሚያ ክልል መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እያበቃ መሆኑ ተገለጸ። በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የጎሎልቻ የመስኖ ግድብ የፌዴራል እና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ እንደገለጹት የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ፕሮጀክቶች በብዛትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እያበቃ ነው። በዚህም በክልሉ ካለፉት አምስት አመታት ወዲህ የተጀመሩ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት በመገንባት ለማጠናቀቅ እንደተቻለም አመልክተዋል። ለአገልግሎት የበቁ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችም የህዝቡን ተጠቃሚነት በማሳደግ የብልጽግና ጉዞን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ናቸው ብለዋል። ህብረተሰቡም የልማት ፕሮጀክቶችን በመጠበቅና በመንከባከብ የበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበት አመልክተዋል። በዛሬው ዕለት የተመረቀው የጎሎልቻ መስኖ ግድብም በክልሉ በመገንባት ላይ ካሉ 73 የመስኖ ፕሮጀክቶች አንዱና ትልቁ እንደሆነ ተናግረዋል። የክልሉ መስኖና አርብቶ አደር ቢሮ ሀላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ በበኩላቸው በክልሉ በግንባታ ላይ ከሚገኙ የመስኖ ግድብ ፕሮጀክቶች ውስጥ ግማሽ የሚሆኑት ተጠናቀው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ መጀመራቸውን አስታወቀዋል። በክልሉ ዝናብ አጠር አካባቢዎች ካለፉት አምስት አመታት ወዲህ 73 የመስኖ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው አብዛኞቹም በምዕራብ ሐረርጌና ቦረና ዞኖች አርብቶ አደር አካባቢዎች እየተገነቡ እንደሚገኙ ገልፀዋል። ከእነዚህም 33 የሚሆኑት ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው አገልግሎት መጀመራቸውን ጠቁመው የተቀሩትን የመስኖ ግድብ ፕሮጀክቶች ፍጥኖ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል። በዛሬው ዕለት የተመረቀው የጎሎልቻ መስኖ ግድብ በአካባቢው ለሚገኙ 2 ሺህ በላይ አባወራ ቤተሰቦችን የሚያገለግል እና አንድ ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የማልማት አቅም እንዳለው አመልክተዋል፡፡ የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ኢክራም ጠሀ በበኩላቸው መንግስት በዞኑ ዝናብ አጠር አካባቢዎች የገነባቸው የመስኖ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን አኗኗር እየለወጡ ነው ብለዋል። አርብቶ አደሩ በአንድ ቦታ ተረጋግቶ እንዲኖርና በግብርናው በስፋት እንዲሳተፍ እያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል። በዞኑ የሌሎች ሶስት የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ የዞኑ አስተዳደር ያልተቋረጠ ድጋፍ እንደሚሰጥ ተናግረዋል። በቦርዶዲ ወረዳ ጎሎልቻ ቀበሌ አርብቶአደሮች በሰጡት አስተያየት የግድቡ መገንባት ለእንስሳት ውሀ ፍለጋ የሚሄዱትን ረጅም ርቀት አስቀርቶላቸዋል። መንግስት የአርብቶአደሩን ችግር በመረዳት እያደረገላቸው ላለው ድጋፍ አመስግነዋል።
በመስከረም ወር ለሚከበሩ የህዝብና የአደባባይ በዓላት አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል-የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር
Sep 19, 2025 98
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፦በመስከረም ወር የሚከበሩ የህዝብና የአደባባይ በዓላት በድምቀት እንዲከበሩ አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ገለፀ። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማህዲ በመስከረም ወር የሚከበሩ የህዝብ በዓላት አከባበርን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በመስከረም ወር የሚከበሩ በርካታ የህዝብና የአደባባይ በዓላትን በደመቀና በተሳካ ሁኔታ ለማክበርና ለማስተዋወቅ የሚያስችሉ ዝግጅቶች ተደርገዋል ብለዋል። እነዚሁ የህዝብ በዓላት ሀገራዊ እድገትን ለማምጣት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስርን የሚያጠናክሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በመስከረም ወር ከሚከበሩ የህዝብና የአደባባይ በዓላት መካከል የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላትን ጨምሮ የብሔር ብሔረሰቦች የዘመን መለወጫ በዓላት እንደሚገኙበት ተናግረዋል፡፡ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የህዝብ በዓላቱን በማልማትና በማስተዋወቅ እሴታቸው ተጠብቆ በድምቀት እንዲከበሩ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በዓላቱ ማህበራዊ መስተጋብርን የሚያጠናክሩ ወሳኝ የህዝብ ኩነቶች በመሆናቸው ለስኬታማነታቸው በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ሁሉም ክብረ በዓላት፤ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ይዘታቸውን ሳይለቁ የማህበረሰቡን አብሮነት በሚያጠናክር መልኩ ማክበር እንደሚገባ ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የተናገሩት፡፡ ክብረ በዓላቱን በሀገር አቀፍ፥ በአህጉር አቀፍ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ ሀገራዊ ገፅታን ለመገንባት ከመገናኛ ብዙሃን ብዙ ስራ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡
ኢኮኖሚ
የጣና ሐይቅ ገዳማትና አዋሳኝ ውኃ አዘል መልከዓ-ምድርን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ ነው
Sep 19, 2025 104
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፡- የጣና ሐይቅ ደሴተ ገዳማትና አዋሳኝ ውኃ አዘል መልከዓ-ምድር የባህልና የተፈጥሮ መካነ-ቅርስ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን የቅርስ አሥተዳደር ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ፀሐይ እሸቴ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ቅርሱ በፈረንጆቹ ሐምሌ 2026 ዓ.ም በኮሪያ ሪፐብሊክ ቡሳን ከተማ በሚካሄደው የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ኮሚቴ 48ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ እንደሚመዘገብ ይጠበቃል። ለቅርሱ ምዝገባ አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎች አካል የሆነው የምዝገባ ሠነድ ቀደም ሲል ለዩኔስኮ ተልኮ ተቀባይነት ማግኘቱንም አስታውሰዋል። እንዲመዘገብ ከተጠየቀው ቅርስ ጋር በተያያዘ ሠነዱ ለጉባዔው ከመቅረቡ በፊት መከናወን ያለባቸው አስገዳጅ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በቀረበው የምዝገባ ሠነድ መሠረት የቅርሱን ይዘት እና ቅርሱ የሚገኝበትን ሁኔታ ለመገምገም በቅርቡ የዩኔስኮ ልዑክ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣም ጠቁመዋል። የልዑካን ቡድኑ አባላት ከዓለም አቀፍ የመታሰቢያ ሐውልቶች እና ስፍራዎች ምክር ቤት እና ከዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ቅርስ ጥበቃ ኅብረት የተውጣጡ ከፍተኛ የዘርፉ ምሁራን መሆናቸውን አመላክተዋል። እስካሁን ኢትዮጵያ 12 የሚዳሰሱ ቅርሶችን በዓለም አቀፍ ቅርስነት ማስመዝገቧንም አውስተዋል።
በጠንካራ አንድነት ያሳካነውን ግዙፍ ፕሮጀክት በሌሎች ዘርፎች ላይም ለመድገም ቁርጠኞች ነን-የህዝባዊ ሰልፍ ታዳሚዎች
Sep 19, 2025 130
ቦንጋ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ) :- በጠንካራ አንድነት ያሳካነውን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሌሎች የልማት ዘርፎች ለመድገም ቁርጠኛ ነን ሲሉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቦንጋ ከተማ የህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ታዳሚዎች ገለፁ። የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ክልል አቀፍ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በቦንጋ ከተማ ተካሄዷል። የሰልፉ ታዳሚዎች ፤ በጠንካራ አንድነት ያሳካነውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሌሎች የልማት ዘርፎች ለመድገም ቁርጠኛ ነን ሲሉ ገልጸዋል። በክልሉ ከቤንች ሸኮ ዞን የመጡት አቶ ወልደየስ ዘለቀ እና ከሸካ ዞን የመጡት ኢንስፔክተር ደመረ አገሎ የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ አንድ ከሆንን የማንወጣው ነገር እንደሌለ ማሳያ ነው ብለዋል። የትውልዱ ኩራትና ዳግማዊ አድዋ የሆነውን የህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማጠናቀቅ ያሳየነውን ድጋፍና ህብረት በሌሎች ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ስራዎች ላይ ለመድገም ቁርጠኛ ነን ብለዋል። ዳግማዊ አድዋ በዘመናችን ተፈፅሞ በማየታችን ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል ያሉት የቦንጋ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ሀና ወልደማሪያም እና ከኮንታ ዞን የመጡት ሻምበል ጀበሌ ዱላ ናቸው። በቀጣይም ኢትዮጵያ የሰነቀችው ራዕይ ተሳክቶ ለማየት እንደሀገር የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል። በህዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ "የህዳሴው ግድብ የህብረታችን አርማ የብልፅግናችን አሻራ ነው" ብለዋል። በጋራ መቆማችን ውስብስብ ችግሮችን ተሻግረን ትልልቅ የልማት ውጥኖችን ማሳካት እንደሚቻል ያረጋገጠ ነው ያሉት ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ከተባበርንና በጋራ ከቆምን ከከፍታ ጉዟችን የሚያስቆመን ኃይል የለም ሲሉም ተናግረዋል። ግድቡ በላባችን፣ በደማችንና በገንዘባችን ያፀናነው ሕያው የምህንድስና ጥበብና የማህበረሰብ የወል ቅርስ ነው በማለት ይህን ግዙፍ ፕሮጀክት በማጠናቀቅ ያሳየነውን ስኬት በሌሎች ላይም እንደግማለን ሲሉ አረጋግጠዋል። በቦንጋ ከተማ በተካሄደው ክልል አቀፍ የደስታ መግለጫ ሰልፍ ላይ የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ ከሁሉም ዞኖች የተወጣጡ የህብረተሰብ ተወካዮችና የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በሲዳማ ክልል ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው
Sep 19, 2025 106
ሀዋሳ ፤ መስከረም 9/2018(ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያመጡ መሆኑን የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሀም ማርሻሎ ተናገሩ ፡፡ የሲዳማ ክልል ገንዘብ ቢሮ የሴክተር ጉባኤ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል ፡፡ በጉባኤው ላይ የተገኙት የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሀም ማርሻሎ፤ በክልሉ ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብና በማስተዳደር ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይ በ2017 በጀት ዓመት ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የክልሉን አብዛኛውን ወጪ በውስጥ አቅም ለመሸፈን በተሰራው ሥራ ከ50 በመቶ በላይ የሚሆነውን ወጪ መሸፈን እንደተቻለ አስረድተዋል፡፡ የተሰበሰበውን ሀብት በቀጥታ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ተግባራት ላይ ለማዋልም በርካታ ሥራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመስኖ፣ የመንገድ፣ የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች መሠረተ ልማት ግንባታዎችን በማከናወን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል፡፡ ለእነዚህ ሥራዎች የተመደበው ሀብት ለታለመለት ዓላማ መዋሉን ለማረጋገጥም የተጠናከረ የኦዲት ሥርዐት በመዘርጋት ውጤታማ ሥራ መስራት ተችሏልም ብለዋል ፡፡ በ2017 በጀት ዓመት በአጠቃላይ ኦዲት ከተፈተሹ 17 የክልል ተቋማት ውስጥ አሥሩ ጤናማ የፋይናንስ ሥርዐት እንዳላቸው መረጋገጡን ጠቅሰው በሰባቱ ደግሞ የታዩ ጥቃቅን ጉድለቶች እንዲታረሙ መደረጉን አብራርተዋል ፡፡ የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥን በመዘርጋት የተቀላጠፈ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በመስጠት ገቢ አሰባሰብን ለመለወጥ በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል፡፡ የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሌ ሀርሲሳ በክልሉ ባለፉት አምስት ዓመታት የፋይናንስ ሥርዐት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያስችሉ የአሰራር ሥርዐትና የሕግ ማዕቀፎች ማሻሻያ ሲደረግ መቆየቱን አውስተዋል፡፡ በ2018 የኢሌክትሮኒክ የመንግስት ግዢ እና የኤሌክትሮኒክ ክፍያ ሥርዐትን ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል። በጉባኤው ላይ የክልል ፣ የዞን እንዲሁም የከተማ አስተዳደርና የወረዳ አመራሮችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል ፡፡
በህገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ተግባር የተሰማሩ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ
Sep 19, 2025 234
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018(ኢዜአ)፦ በህገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ተግባር ላይ የተሰማሩ 123 ተጠሪጣሪዎች የባንክ ሂሳብ እንዲታገድ ተደረገ። ህጋዊና መደበኛ የባንክ ስርዓትን ወደጎን በመተው በህገ-ወጥ እና ትይዩ ገበያ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል ላይ የተሰማሩ አካላት ላይ እርምጃ መወሰዱ እና ሌሎች ላይ ደግሞ የተጠናከረ ክትትል እየተደረገ መሆኑ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት በቅርቡ መግለፁ ይታወሳል። በዚህም የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መግለጫ መሠረት በተለያየ ደረጀ በህገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ድርጊት ላይ የተሰማሩ የ123 ተጠርጣሪዎች የገንዘብ እንቅስቃሴ በዛሬው ዕለት ታግዶ የህግ ተጠያቂነት ለማረጋገጥ በሂደት ላይ ይገኛል። አገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በርካታ ሰው የውጭ ምንዛሪ አገልግሎትን በህጋዊ መንገድ እያካሄደ በመሆኑ በእጅጉ የሚበረታታ መሆኑም ተገልጿል። ነገር ግን አንዳንድ አካላት አሁንም ከጥቁር ገበያ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ድርጊት ለማትረፍ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆናቸውን በክትትል መረጃዎች መረጋገጡም ተገልጿል። በተጨማሪም አንዳንድ የባንክ ባለሙያዎች በጥቁር ገበያ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ድርጊት ውስጥ ተሳትፎ ያላቸው መሆኑ የክትትል መረጃው ውጤት የሚያመላክት በመሆኑ ተጨማሪ ምርመራ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመደገፍ ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል ይህ የወንጀል ድርጊት አንዱና ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የህገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ ተግባር እና ሌሎች መሰል ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ ቁጥር 780/2005 መሠረት የወንጀል ድርጊቱ ላይ ተሳታፊ በሆኑት ላይ ተገቢው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ አገልግሎቱ በልዩ ትኩረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮ-ሰርት ከአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅና የሙስሊም ትብብር ድርጅት አባል ሀገራት መካከል በተካሄደ የሳይበር መከላከልና ማጥቃት አቅም አሽናፊ ሆነ
Sep 19, 2025 94
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ):- በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የሳይበር አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ ማዕከል ከአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እንዲሁም ከሙስሊም ትብብር ድርጅት አባል ሀገራት ከተሳተፉበት የሳይበር መከላከልና ማጥቃት ውድድር አሸናፊ መሆኑ ተገለጸ። ኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ለኢዜአ በላከው መግለጫ ለአምስት ቀናት በሞሮኮ ራባት በተከናወነው የሳይበር ደህንነት ሳምንትን ተያይዞ በተከናወነ ውድድር ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ የሳይበር መከላከል ላይ የሚሰሩ ተቋማት ተሳትፈዋል። በተከናወነው ውድድር ከ30 በላይ ከሙስሊም ትብብር ድርጅት፣ ከአፍሪካና ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የተውጣጡ የሳይበር መከላከል ማዕከላት መሳተፋቸውም ተገልጿል። ተቋማቱ ባደረጉት የሳይበር መከላከልና ማጥቃት ውድድር የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ኢትዮጵያን በመወከል በአንደኝነት ማጠናቀቁን ጠቅሷል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር በሳይበር አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ ማዕከል አማካኝነት የሀገራችንን የዲጂታል ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ 24/7 በተጠንቀቅ የሚሰራና የሀገራችንን የሳይበር ምህዳር የሚጠብቅ ተቋም ነው። የተገኘው ውጤትም ለቀጣይ ስራዎች መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑን አስታውቋል። ከኢትዮጵያ በመቀጠል የካዛኪስታን የሳይበር አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ ማዕከል፣ የፓኪስታን ብሔራዊ የሳይበር ወንጀል ምርመራ ኤጀንሲ፣ ኤል ዋይ እንዲሁም የግብጽ የፋይናንሺያል የሳይበር ክስተት ምላሽ ቡድን ከሁለተኛ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ማጠናቀቃቸውም ተጠቅሷል።
የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ቴክኖሎጂን በቀላሉ ለመላመድ አግዞናል - የስልጠናው ተሳታፊዎች
Sep 19, 2025 97
ባህር ዳር፤ መስከረም 9/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የፈጠራ ስራን የበለጠ ለማዳበርና ቴክኖሎጂዎችን በቀላሉ ለመለማመድ እድል እንደፈጠረላቸው ስልጠናውን የወሰዱ የባህር ዳር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መምህራን ገለጹ። የኮሌጁ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምህር ልጅዓለም መንግስት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ስልጠናው የፈጠራ አቅምንና አማራጭ የስራ ዕድሎችን ማስፋት የሚያስችል ነው። ስልጠናው በበይነመረብ የሚሰጥና የዘመኑ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የደረሰበትን ነባራዊ ሁኔታ ለማስገንዘብና የበለጠ ለማወቅ ተነሳሽነትን የፈጠረ ነው ብለዋል። መተግበሪያዎችን በራስ አቅም መፍጠር የሚያስችል ክህሎት እና እውቀት የሚያስጨብጥና የአስተሳሰብ አድማስን ለማስፋት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አንስተዋል። ስልጠናው ፋንዳሜንታል ፕሮግራሚንግ፣ አንድሮይድ ዴቭሎፕመንት፣ አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ እና መሰል ዘመኑ የሚጠይቀውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀት እና ክህሎት የሚያስጨብጡ ርዕሰ ጉዳዮች የተካተቱበት መሆኑን ተናግረዋል። ስልጠናው በቦታ ሳይገደቡ እጅ ላይ ባለ ስልክ ሳይቀር የሚሰጥ በመሆኑ የዕድሉ ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የኮሌጁ ትምህርትና ስልጠና ምክትል ዲን ባንታየሁ ስንቴ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ዓለም አቀፍ ቴክኖሎጂዎችን ለመረዳትና የበለጠ አስፍቶ ለማሰብ የሚያግዝ በመሆኑ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ መምህራን አቅማቸውን ለማጎልበት ይህን እድል ፈጥነው መጠቀም ይገባቸዋል ብለዋል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ ዘመነ አሰፋ እንዳሉት፤ ወጣቱ የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠናን በመከታተል ከዲጂታል ገበያው ተጠቃሚ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ ነው። ባለፈው ዓመት ለ7ሺህ 596 ወጣቶች ስልጠናውን ለመስጠት ታቅዶ ወደ ስራ እንደተገባ ገልጸው 7ሺህ 652 ወጣቶችን የስልጠናው ተጠቃሚ በማድረግ ከዕቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን አስረድተዋል። የዲጂታል ኢኮኖሚው ስርዓት እየፈጠነ በመሆኑ ዓለም አቀፍ አማራጮችን ለማስፋት የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠናን መጠቀም ወቅቱ የሚጠይቀውን እውቀት ለመገብየት ያስችላል ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመት ከ8ሺህ በላይ ወጣቶች የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የኢትዮጵያን የኒውክሌር ቴክኖሎጂ የመጠቀም እንቅስቃሴ እንደሚደግፍ ገለጸ
Sep 18, 2025 275
አዲስ አበባ፤ መስከረም 8/2018 (ኢዜአ)፦ዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለመጠቀም የጀመረችውን እንቅስቃሴ እንደሚደግፍ ገልጿል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በቪየና ኦስትሪያ እየተካሄደ ካለው 69ኛው የIAEA መደበኛ ጉባኤ ጎን ለጎን ከዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ማርያኖ ግሮሲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይቱ ኢትዮጵያ በምታካሂደው ሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል ፕሮግራም በሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ስለሚያደርጋቸው ድጋፎች ያተኮረ ነው። በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት÷ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ለኢትዮጵያ የካንሰር ማከሚያ መሳሪያ ድጋፍ ማድረጋቸውን አመስግነው፤ የሰው ኃይል አቅም ግንባታ ላይ ኤጀንሲው የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሰላማዊ ኒውክሌር ኢነርጂ ፕሮግራሞችን እውን ለማድረግ መሠረት በመጣል ላይ መሆኗን እና ወደ ትግበራ ለመግባትም ሰፊ ጥረት እያደረገች መሆኗን አብራርተዋል። በዚህም ብሄራዊ የኒውክሌር ኃይል ግንባታ ላይ የቴክኒክ ድጋፍ እና የእውቀት ሽግግር ማድረግ ወሳኝ በመሆኑ ኤጀንሲው ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ በግብርና እና ጤና ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ ከኤጀንሲው ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚፈልጉም መግለፃቸውን ፋና ዲጂታል የሚኒስቴሩን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋዬ ዓለምነውን ጠቅሶ ዘግቧል። ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም የጀመረችውን የቁጥጥር ማዕቀፍ ለማጠናከር ጉልህ ሚና እየተወጣች መሆኗን የገለጹት ሚኒስትሩ ይህንንም በይበልጥ ለማጠናከር የኤጀንሲው ድጋፍ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። ራፋኤል ማርያኖ ግሮሲ በበኩላቸው በቅርቡ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸው ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ መንገድ ለመጠቀም የጀመረችውን እንቅስቃሴ ኤጀንሲ እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል።
የጥራት አመራር ዓለም አቀፍ ዕውቅናዎች የኢትዮጵያ የከፍታ ህልም የማሳኪያ መንገዶች ናቸው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Sep 18, 2025 187
አዲስ አበባ፤ መስከረም 8/2018(ኢዜአ)፦ የጥራት አመራር ዓለም አቀፍ ዕውቅናዎች ኢትዮጵያ ከፍታዋን ለማረጋገጥ የያዘችውን ትልም ማሳኪያ መንገዶች መሆናቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በትምህርት ሥራ አመራር ሥርዓት ISO-21001-2018 ዓለም አቀፍ ዕውቅና ማግኘቱን ተከትሎ የምሥክር ወረቀት ርክክብ ተካሂዷል። 57 ዓመታትን ያስቆጠረው ኢንስቲትዩቱ ለሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት የላቀ ሚና መጫወቱ ተገልጿል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ኢትዮጵያ በየዘርፎቹ እያካሄደች በሚገኘው ሪፎርም ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች የከፍታዋ መጀመሪያ ምልክቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። የሀገራችን ተቋማት የዓለም አቀፍ የጥራት አመራር ሥርዓት ዕውቅናዎች እያገኙ መሆናቸው የማንሰራራት ጉዞዋ ማሳያ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ሀገር አቀፍ የአስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ እየተደረገ ያለው ሪፎርም የሀገረ መንግስት ግንባታ አካል መሆኑንም ተናግረዋል። በዘርፉ እየተገኙ ያሉ የጥራት አመራር ዓለም አቀፍ ዕውቅናዎች ኢትዮጵያ ከፍታዋን ለማረጋገጥ የያዘችው ትልም የማሳኪያ መንገድ መሆኑንም አስታውቀዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርን ጨምሮ በስሩ ያሉ ተቋማት 16 ዓለም አቀፍ ዕውቅናዎች ማግኘታቸውንም አንስተዋል። የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ተቋማት የተገልጋዩን እርካታ ማረጋገጥ አለባቸው ያሉት ሚኒስትሯ በቱሪዝም ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ሀገራዊ ፋይዳው የላቀ መሆኑንም ጠቁመዋል። የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የእውቅ ሙያተኞች መፍለቂያ መሆኑን በማውሳት፥ ኢትዮጵያ ያላትን ባህልና እሴት በአግባቡ በማስተዋወቅና ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት የበለጠ እንዲተጋ አስገንዝበዋል። የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ነጋሽ በበኩላቸው፤ ኢንስቲትዩቱ ለኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት የድርሻውን ሲወጣ መቆየቱን አውስተዋል። መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ተከትሎ ከስልጠና ባለፈ ችግር ፈቺ ምርምሮችን እያደረገ መሆኑንም ነው ያነሱት። በዚህም የተገልጋዩን እርካታ መጨመር የሚችል ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሠረት በቀለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቱሪዝም የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ዋነኛ መሰረት የሚሆን ዘርፍ ነው ብለዋል። የሰው ሀብት፣ የመሰረት ልማት እንዲሁም የአሰራር ስርዓት መዘመን ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር መዓዛ አበራ፤ የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሥራ በመስራቱ የዕውቅና ምሥክር ወረቀት ማግኘቱን ገልጸዋል። መንግስት ለምርትና አገልግሎት ጥራት በሰጠው ትኩረት የጥራት መንደር ገንብቶ ምርትና አገልግሎቶች ደረጃቸውን እንዲጠብቁ እያደረገ መሆኑንም አክለዋል። የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በትምህርት ሥራ አመራር ሥርዓት ISO-21001-2018 ዓለም አቀፍ ዕውቅና ማግኘቱን አንስተዋል።
ስፖርት
በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ፍጻሜን የስፔን እና የብራዚል አትሌቶች አሸነፉ
Sep 20, 2025 36
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2018 (ኢዜአ)፦ በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ፍጻሜን የስፔን እና የብራዚል አትሌቶች አሸንፈዋል። በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ፍጻሜ የስፔኗ አትሌት ማሪያ ፔሬዝ አሸንፋለች። አትሌቷ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 1 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ ፈጅቶባታል። ማሪያ እ.አ.አ በ2019 በሀንጋሪ ቡዳፔስት በተካሄደው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በተመሳሳይ ርቀት አሸናፊ እንደነበረች የሚታወስ ነው። አትሌቷ የቡዳፔስት ወርቋን በቶኪዮ ደግማለች። የሜክሲኮዋ አትሌት አሌና ጎንዛሌዝ 1 ሰዓት ከ26 ደቂቃ ከ06 ሴኮንድ፣ ጃፓናዊቷ አትሌት ናናኮ ፉጂ 1 ሰዓት ከ26 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል። ኢትዮጵያን ወክላ የተወዳደረችው ስንታየሁ ማስሬ አምስት ኪሎ ሜትር ላይ ውድድሩን አቋርጣለች። በተመሳሳይ የወንዶች የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ፍጻሜ የብራዚሉ ካዮ ቦንፊ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ አሸንፏል። በወንዶች ቻይናዊው ዣኦዣኦ ዋንግ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ43 ሴኮንድ ሁለተኛ፣ ስፔናዊው ፖል ማክግራዝ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ45 ሴኮንድ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ኢትዮጵያን ወክሎ የተወዳደረው ምስጋና ዋቁማ 1 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ17 ሴኮንድ 18ኛ ወጥቷል። ከሌሊቱ 9 ሰዓት ከ55 ላይ በተካሄደው የወንዶች የ20 ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር ፍጻሜ ፍጻሜ የብራዚሉ ካዮ ቦንፊም 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ አንደኛ ወጥቷል። ቻይናዊው ዣኦዣኦ ዋንግ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ43 ሴኮንድ ሁለተኛ፣ ስፔናዊው ፖል ማክግራዝ 1 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ45 ሴኮንድ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ኢትዮጵያን ወክሎ የተወዳደረው ምስጋና ዋቁማ 1 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ17 ሴኮንድ 18ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል።
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ይካሄዳሉ
Sep 19, 2025 89
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፦ በጃፓን ቶኪዮ እየተካሄደ የሚገኘው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ይደረጋሉ። ከሌሊቱ 7 ሰዓት ከ30 በሴቶች የ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር አትሌት ስንታየሁ ማስሬ ትወዳደራለች። አትሌት ስንታየሁ በውድድሩ ላይ እንድትሳተፍ የተመረጠችው እ.አ.አ በ2024 በካሜሮን ዱዋላ በተካሄደው 23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በርቀቱ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘቷን ተከትሎ ነው። ስንታየሁ በካሜሮኑ ውድድር 1 ሰዓት ከ37 ደቂቃ ከ46 ሴኮንድ አንደኛ በመውጣት በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቷን ማስመዝገቧ የሚታወስ ነው። አትሌቷ እ.አ.አ በ2023 በጋና በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ጨዋታዎች በ20 ኪሎ ሜትር ርምጃ ተወዳድራ የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። እ.አ.አ በ2011 በኮትዲቭዋር አቢጃን በተደረገው ራተኛው ከ18 እና 20 ዓመት በታች የአፍሪካ ታዳጊዎች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ10 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ሶስተኛ በመውጣት የነሐስ ሜዳሊያ ማግኘቷ የሚታወስ ነው። በተጨማሪም ስንታየሁ እ.አ.አ በ2018 በአልጄሪያ በተካሄደው ሶስተኛ የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታ በአምስት ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። ከሌሊቱ 9 ሰዓት ከ55 በሚደረገው የወንዶች የ20 ኪሎ ሜትር ርምጃ ፍጻሜ አትሌት ምስጋና ዋቁማ ኢትዮጵያን ወክሎ ይወዳደራል። አትሌት ምስጋና በውድድሩ ላይ እንዲሳተፍ የተመረጠው በ20 ኪሎ ሜትር የወንዶች ርምጃ ዓለም አቀፍ የደረጃ ሰንጠረዥ 14ኛ ላይ በመገኘቱ ባገኘው የተሳትፎ ኮታ ነው። ምስጋና እ.አ.አ በ2024 በፓሪስ በተካሄደው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች በ20 ኪሎ ሜትር የወንዶች ርምጃ ውድድር ስድስተኛ መውጣቱ ይታወሳል። በወቅቱ 1 ሰዓት ከ19 ደቂቃ ከ31 ሴኮንድ የገባበት ጊዜ የርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቱ ነው። አትሌቱ እ.አ.አ በተርኪዬ አንታሊያ በተካሄደው የዓለም የርምጃ ውድድር ሻምፒዮና 1 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ51 ሴኮንድ 10ኛ ወጥቷል። እ.አ.አ በ2023 በጋና በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ጨዋታዎች እና እ.አ.አ በ2024 በካሜሮን ዱዋላ በተካሄደው 23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በርቀቱ የወርቅ ሜዳሊያዎችን አግኝቷል። በርምጃ ውድድሮች ስንታየሁ ማስሬ እና ምስጋና ዋቁማ ጠንካራ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
ወላይታ ድቻ እና አል-ኢትሃድ ነጥብ ተጋርተዋል
Sep 19, 2025 116
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፦ ወላይታ ድቻ 2025/26 የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታ ከሊቢያው አል-ኢትሃድ ጋር ያደረገው ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። ጨዋታው በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ተካሂዷል። ወላይታ ድቻ እና አል-ኢትሃድ የመልስ ጨዋታቸውን መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም ያደርጋሉ። ቡድኑ በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈ በመጨረሻው ዙር ከግብጹ አል ማስሪ ጋር ይገናኛል። ወላይታ ድቻ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ ነው።
በ800 ሜትር የሴቶች ማጣሪያ ጽጌ ዱጉማ እና ወርቅነሽ መሰለ ለፍጻሜ ሳያልፉ ቀሩ
Sep 19, 2025 95
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፦ በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ከቀትር በኋላ በተደረገው የ800 ሜትር ሴቶች ማጣሪያ ጽጌ ዱጉማ እና ወርቅነሽ መሰለ ለፍጻሜ ማለፍ አልቻሉም። በምድብ ሁለት የተወዳደረችው ጽጉ ዱጉማ አምስተኛ፣ በምድብ ሶስት የተወዳደረችው ወርቅነሽ መሰለ ዘጠነኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል። በሶስት ምድብ በተደረገው ማጣሪያ ከእያንዳንዱ ምድብ አንደኛ እና ሁለተኛ የወጡ አትሌቶች የፊታችን እሁድ ለሚካሄደው የፍጻሜ ውድድር በቀጥታ አልፈዋል። በተጨማሪም ሁለት ፈጣን ሰዓት ያላቸው ተወዳዳሪዎች ፍጻሜውን ተቀላቅለዋል።
አካባቢ ጥበቃ
የአዲስ አበባ ዲክላሬሽን አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች የመሪነት ሚና እንድትጫወት የሚያስችላት ነው
Sep 19, 2025 142
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018 (ኢዜአ)፦በሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ የጸደቀው የአዲስ አበባ ዲክላሬሽን አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች የመሪነት ሚና እንድትጫወት የሚያስችላት መሆኑን የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)ገለጹ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመተባበር ያካሄደው ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አፈፃፀምና የተገኙ ውጤቶችን አስመልክተው የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው ጉባኤው አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ተጎጂ ብቻ ሳትሆን የመፍትሄ አካል መሆኗን ያሳየችበት ነው ብለዋል። በተጨማሪም በጉባዔው አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ለመፍታት ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች መሆኑን ማስገንዘብ መቻሉን አመላክተዋል። ጉባኤው የአፍሪካን የጋራ ድምጽ የያዘው የአዲስ አበባ ዲክላሬሽን በማጽደቅ መጠናቀቁን ጠቅሰው ዲክላሬሽኑ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች የመሪነት ሚና እንድትጫወት የሚያስችላት መሆኑን ተናግረዋል። ለአፍሪካ የተሰጠውን ያልተገባ ትርክት በመቀየር እየወሰደቻቸው ያሉ ተጨባጭ እርምጃዎችን ማሳወቅ መቻሉን ተናግረዋል። ይህም በአፍሪካ መሪዎችና ባስተላለፏቸው ውሳኔዎች በጉልህ መመላከቱን ገልጸዋል። ለአብነትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው የመክፈቻ ንግግራቸው አፍሪካ የምትፈልገው እርዳታና ችሮታ ሳይሆን ኢንቨስትመንት እንደሆነ መግለጻቸውን አስታውሰዋል። የአረንጓዴ ማዕድናት እና ንጹህ የኢነርጂ ተደራሽነት የሚያሰፉ ስትራቴጂዎችን ማጠናከር ሌላኛው ጉባኤው ከስምምነት ላይ የደረሰበት አጀንዳ መሆኑን ጠቁመዋል። በመሪዎች የተደረጉ ውሳኔዎችን በተመለከተም የአፍሪካ መሪዎች የሚሽን 300 አጀንዳ እና ክሊን ኩኪንግ ኢኒሼቲቭ ተግባራዊ እንዲደረግ ማሳሰባቸውን ገልጸዋል። እንዲሁም አፍሪካ ከአለም አቀፍ የታዳሽ ሃይል ኢንቨስትመንቶች ድርሻ በ2030 ከነበረበት ከ2 በመቶ ወደ 20 በመቶ እንዲያድግ መጠየቃቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአረንጓዴ ማዕድን ስትራቴጂ ትግበራን ማፋጠን እንደሚገባ መወሰናቸውንም አንስተዋል። ከአየር ንብረት ጋር የተገናኙ የጤና ስጋቶች እና በውሃ ወለድ የሚተላለፉ በሽታዎች ስርጭትን ለመፍታት መሪዎች የፋይናንስ ስርዓት ለመመስረት ቃል መግባታቸውን ጠቁመዋል። በርካታ የጎንዮሽ ሁነቶች መካሄዳቸውን ገልጸው፤ ዓለም አቀፍ አጋሮች የፋይናንስ ድጋፎችን ለማድረግም ቃል መግባታቸውን ተናግረዋል። በጉባኤው ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተጽዕኖን መቀነስ ላይ የመሪነት ሚናዋን ለዓለም ማሳየቷን ገልጸው፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የአዲስ አበባው ዲክላሬሽን ላይ ለአፍሪካ በሞዴልነት መጠቀሱን አንስተዋል። በተጨማሪም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ሳምንት በአዲስ አበባ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይህም በመልካም ሁኔታ መካሄዱን እና በዚህም ላይ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ምላሾች ላይ ተሞክሮዋን በስፋት ማካፈሏን ተናግረዋል።
በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አህጉሪቱ የአየር ንብረት ለውጥ የመፍትሔ አካል መሆኗን በግልጽ ማሳየት ችላለች
Sep 19, 2025 118
አዲስ አበባ፤ መስከረም 9/2018(ኢዜአ)፦ በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ አህጉሪቱ የአየር ንብረት ለውጥ የመፍትሔ አካል መሆኗን በግልጽ ማሳየት መቻሏን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ገለጹ። ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፥ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" በሚል መሪ ሀሳብ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመተባበር ያካሄደው ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አፈፃፀምና የተገኙ ውጤቶችን አስመልክተው ፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በዚህም ጉባኤው አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ የመፍትሄ አካል መሆኗን ያሳየችበት እንደሆነ ገልጸዋል። በተጨማሪም አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ለመፍታት ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች መሆኑን ማስገንዘብ መቻሉንም አመላክተዋል። ለአፍሪካ የተሰጠውን ያልተገባ ትርክት በመቀየር እየወሰደቻቸው ያሉ ተጨባጭ እርምጃዎችን ማሳወቅ መቻሉን ሚኒስትሯ ተናግረዋል። ጉባኤው የአፍሪካን የጋራ ድምጽ የያዘው የአዲስ አበባ ዲክላሬሽን በማጽደቅ መጠናቀቁን አመላክተዋል። በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት “Africa Climate Innovation Compact” እና “African Climate Facility” የተሰኙ ኢኒሼቲቮች ይፋ መደረጋቸውን አንስተዋል። በጉባኤው ከ25ሺህ በላይ ልዑካን መሳተፋቸውንና በርካታ የጎንዮሽ ሁነቶች መካሄዳቸውን ገልጸው፤ ዓለም አቀፍ አጋሮች የፋይናንስ ድጋፎችን ለማድረግ ቃል መግባታቸውንም ገልጸዋል። የአረንጓዴ ማዕድናት እና የንጹህ ኢነርጂ ተደራሽነት የሚያሰፉ ስትራቴጂዎችን ማጠናከር ሌላኛው ጉባኤው ከስምምነት ላይ የደረሰበት አጀንዳዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል። በመሪዎች ደረጃም የአየር ንብረት ተጽእኖን መፍታት የሚያስችሉ ውሳኔዎች መተላለፋቸውን ተናግረዋል። በጉባኤው ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተጽእኖን መቀነስ ላይ የመሪነት ሚናዋን ለአለም ማሳየቷን ገልጸው፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀግብር የአዲስ አበባው ድንጋጌ ላይ ለአፍሪካ በሞዴልነት መጠቀሱን አንስተዋል። በተጨማሪም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ሳምንት በአዲስ አበባ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይህም በመልካም ሁኔታ መካሄዱንና በዚህም ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ምላሾች ላይ ተሞክሮዋን በስፋት ማካፈሏን ተናግረዋል።
ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በጋ የሆኑ አካባቢዎች መደበኛ እና ከመደበኛ በታች የዝናብ ስርጭት ይኖራቸዋል
Sep 18, 2025 194
አዳማ ፤ መስከረም 8/2018(ኢዜአ)፦- ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በጋ የሆኑ አካባቢዎች መደበኛ እና ከመደበኛ በታች የዝናብ ስርጭት እንደሚኖራቸው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ የክረምት ወቅት የአየር ጸባይ ትንበያ ግምገማና የበጋ ወቅት የአየር ሁኔታ ጸባይ አዝማሚያ ትንበያ ይፋ ለማድረግ ያዘጋጀው መድረክ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፈጠነ ተሾመ እንዳስታወቁት ኢንስቲትዩቱ የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የአየር ትንበያ መረጃዎችን በወቅቱ ለተጠቃሚዎች እየሰጠ ይገኛል። ትንበያዎቹ ለግብርና፣ ለውሀ ሀብት አስተዳደር፣ ለአደጋ ስጋት ዝግጅት፣ ለጤናና ለአካባቢ ጥበቃ ስራዎች እያገለገሉ መሆናቸውን ገልፀዋል። የትንበያዎቹን ትክክለኛነት ለማሳደግም ሳይንሳዊ ዘዴን በመጠቀም መሰራታቸውን ጠቁመው ይህም የኢንስቲትዩቱን በ2017/18 የክረምት ወቅት የአየር ጸባይ ትንበያ ውጤታማ እንዳደረገው ገልጸዋል። አሁን ላይ ኢኒስቲትዩቱ የበጋ ወቅት ትንበያ መረጃዎችን ለህብረተሰቡና ለተቋማት ይፋ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በጋ በሆኑት የቦረናና ጉጂ ዞኖች፣ ሲዳማና ደቡብ ኢትዮጵያ መደበኛ ዝናብ እንደሚኖራቸው ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። እንዲሁም የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል ደግሞ ከመደበኛ በታች የሆነ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚያገኙ አክለዋል። በሌላ በኩል የምእራብና ደቡብ ምእራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚያገኙ አቶ ፈጠነ ተናግረዋል። ህብረተሰቡ እነዚህን መረጃዎች በመጠቀም የአደጋ ተጋላጭነትን በመቀነስ ስጋቶችን ወደ መልካም አጋጣሚዎች በመቀየር ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ አስገንዝበዋል። የውሀና ኢነርጂ ሚኒስትር (ዶ/ር) ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ መረጃን በማዘመን እየሰጠ ያለው ትንበያ ለተለያዩ ተቋማት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልፀዋል። በተለይ ሴክተር ተኮር መረጃን በወቅቱ ለተጠቃሚዎች በመስጠት የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው ገልፀዋል። በተለይ በውሀ ሴክተሩ የሚቀርቡ መረጃዎችን ሚኒስቴሩ በአግባቡ በመጠቀም የታላቁ የኢትዮጵያ ግድብ የውሀ ሙሌትን በተሳካ ሁኔታ ማከናወኑን ለአብነት ጠቅሰዋል። በመሆኑም የሚሰጡትን ትንበያዎች በአግባቡ በመተንተንና ተግባር ላይ ለማዋል ሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶች እንዲጠቀሙበት ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል። በመድረኩ ላይ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሁሉም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና ምክትል ሰብሳቢዎች፣ የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ናቸው።
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ስትራቴጂዎችን ወደ ተግባር በመቀየር እያከናወነች ያለው ስራ የሚደነቅ ነው -የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከፍተኛ የአየር ነብረት አስተዳደር ባለሙያ
Sep 18, 2025 170
አዲስ አበባ፤ መስከረም 8/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ስትራቴጂዎችን ወደ ተግባራዊ እውነታ በመቀየር እያከናወነች ያለው ስራ የሚደነቅ ነው ሲሉ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከፍተኛ የአየር ነብረት አስተዳደር ባለሙያ ጀምስ ሙሮምቤድዚ ገለጹ። የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሴኤ) ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እያከናወነች ላለው ስራ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ዩኤንኢሴኤ) ከፍተኛ የአየር ነብረት አስተዳደር ባለሙያ ጀምስ ሙሮምቤድዚ የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎችን ለመከላከል አፍሪካ በቀል መፍትሄዎችን የመጠቀም ባህል ሊያድግ እንደሚገባ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል። በዚህ ረገድም አረንጓዴ አሻራ በመላው አፍሪካ በስፋት ሊተገበር የሚገባ ኢኒሼቲቭ ነው ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለንጹህ ኢነርጂ ምንጭነት እና ለዘላቂ የኢንዱስትሪ እድገት ከፍተኛ ሚና እንደሚወጣ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ የካርቦን ልህቀትን በመቀነስ በዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ መስክረዋል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ እድገት ስትራቴጂ ከስነ ምህዳር ማገገም፣ የህዳሴ ግድብ ግንባታ፣ የካርቦት ልህቀት ቅነሳ እና የኤሌክትሪክ መኪኖች አገልግሎት እርምጃዎች ጋር ተዳምሮ ለአረንጓዴ እና ታዳሽ ኃይል ልማት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ስትራቴጂዎችን ወደ ተግባራዊ እውነታ በመቀየር እያከናወነች ያለው ስራ የሚደነቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በአህጉሪቷ ውስጥ ያላት ስትራቴጂካዊ ስፍራ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር በመተባበር የአየር ንብርተ መፍትሄዎችን ለመተግበር ምቹ አጋጣሚ እንደሚፈጥርላትም ነው የገለጹት ከፍተኛ ባለሙያው። የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ መሆኗም የአህጉሪቷ የአየር ንብረት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ማዕከል እንደሚያደርጋት ተናግረዋል። ባለሙያው ኢትዮጵያ እና ኢሴኤ ለረጅም ጊዜ የቆየ አጋርነት እንዳላቸው ገልጸው በአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ እና አቅም ግንባታ የነቃ ተሳትፎ እያደረገ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ኢሲኤ ከኢትዮጵያ ተቋማት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታን እየደገፈ መሆኑን ተናግረዋል። የአየር ሁኔታ ትንበያ እና ቅኝት ስርዓትን ማጠናከር እንዲሁም የአረንጓዴ አሻራ በፖሊሲ እና በትግበራ ደረጃ የመደገፍ ስራ መኖሩንም ጠቅሰዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አፍሪካውያን ለአህጉራቸው ሰላም እና ብልጽግና ያላቸውን ቁርጠኝነት ዳግም ሊያረጋግጡ ይገባል - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Sep 9, 2025 678
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2017(ኢዜአ)፦ አፍሪካውያን ለአህጉራቸው ሰላም እና ብልጽግና ያላቸውን ቁርጠኝነት በማጽናት የተሻለ መጻኢ ጊዜን ለመፍጠር በጋራ እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጥሪ አቀረቡ። የአፍሪካ ህብረት ቀን ዛሬ እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ ሴፕቴምበር 9/1999 በሲርት ድንጋጌ አማካኝነት የተቋቋመበት ቀን የሚታወስበት ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ቀኑን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት አፍሪካውያን ቀኑን ሲዘክሩ የአህጉሪቷን ለውጦች በማክበር እና ለአንድነት፣ ሰላምና ብልጽግና ያላቸውን ቁርጠኝነት ዳግም በማረጋገጥ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል። የህብረቱ መመስረት ውሳኔ ለአፍሪካ ትብብር፣ ትስስር እና አጋርነት መሰረት የጣለ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ቀን የጋራ ጉዟችንን፣ የህዝባችንን አይበገሬነት እና ያጋመደንን የፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ የምናከብርበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ በመልዕክታቸው በአፍሪካ በተለያዩ መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶችን አንስተዋል። በሰላምና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና፣ የታዳሽ ኃይል ልማት፣ ዲጂታል ኢኖቬሽንና የወጣቶችን አቅም በመገንባት የተከናወኑ ስራዎች አፍሪካን በዓለም መድረክ ያላት ሚና እንዲያድግ አስተዋጽኦ ማድረጉን ነው ሊቀ መንበሩ የገለጹት። የአፍሪካ ህብረት ለአጋርነት፣ ትስስር እና ዘላቂ ልማት ያለውን ቁርጠኝነት ጠቅሰው መንግስታት፣ ሲቪክ ማህበረሰቡ፣ የግሉ ዘርፍ እና ወጣቱ ፈተናዎችን በጋራ በመሻገር አጀንዳ 2063 ይዞ የመጣችውን እድሎች እንዲጠቀም ጥሪ አቅርበዋል። ሁሉም አፍሪካውያን ክብራቸው ተጠብቆ የሚኖሩባት እና መጻኢ ጊዜያቸው ብሩህ የሆነች አህጉር እጅ ለእጅ በመያያዝ እንገንባ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በአህጉራዊ ትስስር ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Aug 26, 2025 1327
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በአህጉራዊ ትስስር አጀንዳ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰሩ አስታወቁ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት(ጄኔቫ) የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኛ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሴኤ) ዋና ፀሐፊ ክላቫር ጋቴቴ ጋር ተወያይተዋል። ሁለቱ ወገኖች አፍሪካ በዓለም መድረክ አንድ የጋራ ድምጽ እንዲኖራት ማድረግ ያለውን ወሳኝ ጠቃሜታ አጽንኦት ሰጥተው መክረውበታል። የአፍሪካ ህብረት እና ኢሲኤ በንግድ፣ቀጣናዊ ትስስር እና የአፍሪካ የአዕምራዊ ንብረትን የበለጠ አጀንዳ ማራመድ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት(ጄኔቫ) የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው በሐምሌ ወር 2017 ዓ.ም መሾማቸው የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ህብረት እና ኢሲኤ ትብብራቸውን እ.አ.አ በ1960ዎቹ መግቢያ ላይ መጀመራቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ።
አፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት በትብብር ይሰራሉ
Aug 24, 2025 1141
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 18 /2017 (ኢዜአ)፦አፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት በትብብር እንደሚሰሩ አስታወቁ። ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም(ቲካድ) በዮካሃማ መካሄዱን ቀጥሏል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከፎረሙ ጎን ለጎን ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ፕሬዝዳንት አኪሂኮ ታናካ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የጃይካ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንዲሁም ኢኮኖሚና ማህበራዊን ጨምሮ በአፍሪካ ቁልፍ ዘርፎች እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት አድንቀዋል። ሊቀ መንበሩ እና ፕሬዝዳንቱ የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ያላቸውን የጋራ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ዘጠነኛውን የቲካድ ፎረም መንፈስ ወደ ዘላቂ የኢኮኖሚ ለውጥ በጋራ የመፍጠር ምዕራፍ ማሸጋገር እንደሚገባም አንስተዋል። ከነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው ፎረም የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ፤ የአህጉር በቀል መፍትሄዎች መድረክ
Aug 23, 2025 1176
በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን የአየር ንብረት በርቀት የሚያዩት ስጋት ሳይሆን የዕለት ተዕለት እውነታቸው ነው። በጎርፍ ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች እና ተጠራርገው የሚወሰዱ ንብረቶች፣ በተከታታይ ድርቆች ምክንያት የሚያጋጥመው የምርታማነት መቀነስ የአየር ንብረት ለውጥ ከወለዳቸው ቀውሶች መካከል ይጠቀሳሉ። እነዚህ በተጨባጭ የዜጎችን ኑሮ እየተፈታተኑ ያሉ ችግሮች በአፍሪካ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስነ ምህዳር ላይ ለውጥ እንዲመጣ አስገድደዋል። የድህነት ምጣኔ እና የተፈናቃይ ዜጎች እየጨመረ መምጣት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎችን በተግባር የገለጡ ጉዳዮች ሆነዋል። አፍሪካ ለዓለም የበካይ ጋዝ ልቀት ከአራት በመቶ በታች ድርሻ ቢኖራትም የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳት ከፍተኛ ቀንበር የሚያርፍባት አህጉር ሆናለች። ከሳህል ቀጣና የበረሃማነት መስፋፋት እስከ ምስራቅ አፍሪካ ኃይለኛ ጎርፎች የአህጉሪቷ ዜጎች በጣም ውስን ድርሻ ባላቸው ጉዳይ የቀውሱ ከፍተኛ ሰላባ እየሆኑ ነው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የአስቸኳይ ጊዜ ውስጥ ናት ቢባል ማጋነን አይሆንም። እንደ ዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት መረጃ ከእ.አ.አ 1991 እስከ 2022 ባለው ሶስት አስርት ዓመታት ባሉ እያንዳዱ አስርት ዓመታት በአፍሪካ በአማካይ የ0 ነጥብ 3 ዲግሪ ሴልሺየስ የሙቀት ጭማሪ ተመዝግቧል። እ.አ.አ በ2024 የዓለም ሙቀት በ1 ነጥብ 2 ዲግሪ ሴልሺየስ ጨምሮ በዓለም ታሪክ ከፍተኛው ሙቀት የተመዘገበበት ዓመት ነበር። 2024 በአፍሪካ የሙቀት መጠን 0 ነጥብ 86 በመቶ በመጨመር በአህጉሪቷ ታሪክ ከፍተኛው ሙቀት የተዘመገበበት ዓመት ሆኖም ተመዝግቧል። ከሙቀቱ በአሳሳቢ ሁኔታ መጨመር ባሻገር ድርቅ፣ ጎርፍ እና የምግብ ዋስትና ስጋት ላይ መውደቅ ሌሎች የአፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ናቸው። እ.አ.አ 2024 ደቡባዊ አፍሪካ ክፍል በቅርብ አስርት ዓመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ድርቅ አጋጥሟታል። በድርቁ ምክንያት ዛምቢያ እና ዚምባቡዌ የሰብል ምርታቸው በ50 በመቶ ቀንሷል። በምስራቅ እና ማዕከላዊ አፍሪካ በቅርብ ጊዜ የተከሰቱ ከባድ ጎርፎች ሚሊዮኖችን አፈናቅለዋል፤ የዜጎች ህይወት አመሰቃቅላዋል መሰረተ ልማቶችንም አውድመዋል። የዓለም አቀፉ ሜትሮሎጂ ድርጅት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካን ከሁለት እስከ አምስት በመቶ ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) ወጪ እየወሰደ ይገኛል። አንዳንድ ሀገራት ለአየር ንብረት አስቸኳይ ምላሽ ዘጠኝ በመቶ ጥቅል ሀገራዊ ምርታቸውን ፈሰስ ያደርጋሉ። አፍሪካ በየዓመቱ ከ30 እስከ 50 ቢሊዮን ዶላር ለአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ አቅዶች ትግበራ ቢያስፈልጋትም ከዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ ውስጥ የምታገኘው ገንዘብ ከአንድ በመቶ በታች ነው። የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት የ2024 የአፍሪካ ሪፖርት የአፍሪካ የግብርና ምርታማነት ከእ.አ.አ 1961 በኋላ በ34 በመቶ መቀነሱን ይገልጻል። የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ ሀገራት ምግብ ለመግዛት የሚያወጡት 35 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ወጪ እ.አ.አ በ2025 ማብቂያ ወደ 110 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ከፍ እንደሚል ገልጿል። የበረሃማነት መስፋፋት፣ የብዝሃ ህይወት መመናመን፣ የጤና እክሎች፣ መፈናቀል እና የታሪካዊ ቅርሶች አደጋ ላይ መውደቅ አፍሪካ እየገጠሟት ያሉ የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎች ውጤት ናቸው። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት በየዓመቱ 250 ቢሊዮን ዶላር ቢያስፈልጋትም እያገኘች ያለችው 30 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ስጋት አፍሪካ የጥያቄ አምሮት ኖሮባት የምታነሳው አጀንዳ ሳይሆን የፍትህ እና የህልውናዋ ጉዳይም ጭምር ነው። በአዲስ አበባ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፥ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አህጉሪቷ እየገጠሟት ካሉ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይመክራል። የሀገራት መሪዎች፣ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ወጣቶች እና የግሉ ዘርፍ በአንድነት ይወያያሉ። በጉባኤው ላይ አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በታዳሽ ኢነርጂ፣ ዘላቂ ግብርና እና ተፈጥሮ ተኮር መፍትሄዎች ጨምሮ በአፍሪካ ያሉ አረንጓዴ የመፍትሄ ሀሳቦች የበለ ማላቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሀገራት ተሞክሯቸውን ያቀርባሉ። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ በየዓመቱ የሚያጋጥማትን የ220 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ አቅርቦት ክፍተት መሙላት እና አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም ላይ ምክክር ይደረጋል። በብራዚል ቤለም በሚካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ 30) ጨምሮ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ድርድሮች ላይ የአፍሪካን ፍላጎቶች እና ጥቅሞች ማስጠበቅ የሚያስችል የጋራ እና ጠንካራ አቋም መያዝ ከጉባኤው የሚጠበቅ ውጤት ነው። የአፍሪካ ሀገራት በጉባኤው ላይ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል የሚያስችሉ ተጨባጭና መሬት ላይ የወረዱ እቅዶቻቸው ላይ የሚያቀርቡ ሲሆን የገቡትን ቃል ኪዳን ወደ ተግባር መቀየራቸውን የሚከታተል የቁጥጥር ስርዓት ትግባራትን የሚያጠናክሩባቸው መንገዶችን በማቅረብ በአጠቃላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ቃልኪዳናቸውን ዳግም ያድሳሉ። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች ገፈት ቀማሽ ሳትሆን የመፍትሄዎች እና የአይበገሬነት ስራዎች ማሳያም ናት። የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ እና አከባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የኬንያ የእንፋሎት እና የፀሐይ ኃይል ኢንሼቲቮች እንዲሁም የሞሮኮ ኑር ኦውርዛዛቴ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አረንጓዴ ልማት ሊሆን የሚችል ብቻ ሳይሆን በተጨባጭ የሚሳካ መሆኑን አፍሪካ ማረጋገጫ እንደሆነች በግልጽ የሚያመላክት ነው። አፍሪካ ከዓለም ዋንኛ በካይ ጋዝ ለቃቂ ሀገራት ገንዘብ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ሀገር በቀል የፋይናንስ እና ሀብት ማሰባሰብ አቅማቸውን የበለጠ ማሳደግ ይጠበቅባታል። የአዲስ አበባው ጉባኤም የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ አቅርቦታቸውን እንዲጨምሩ ጥሪ የሚቀርብበት ነው። አፍሪካውያን እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ ከንግግር ያለፉ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን በመተግበር አይበገሬ አቅም ሊገነቡ ይገባል። የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ሀገር በቀል የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎችን ከዓለም አቀፍ አጋርነት ጋር ከማዛመድ አኳያ ያላው ሚና ወሳኝ የሚባል ነው። ጉባኤው አፍሪካ ከአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ትርክት ወደ መፍትሄ አፍላቂነት እና የግንባር ቀደም ሚና አበርካችነት ለመሸጋገር እንደ መስፈንጠሪያ የሚያገለግል ትልቅ እድል ነው። የአዲስ አበባው ጉባኤ ከስብስባ ባለፈ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ቆርጣ ለተነሳችበት የተግባር ምላሽ ጉዞ እና የዓለም አቀፍ ተጠያቂነት መረጋገጥ የጋራ ትግል ውስጥ ትልቅ እጥፋት ሊሆን ይችላል።
ሐተታዎች
ከጉባ እስከ ዓለም መድረክ፤ የዓለም አይኖች ያረፉበት የሕዳሴ ግድብ
Sep 13, 2025 551
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም መመረቁ ይታወቃል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ (ዶ/ር)፣ የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦመር ጊሌህ፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ (ዶ/ር)፣ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት፣ የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ አሞር ሞትሊ፣ የእስዋቲኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሴል ሚሶ ድላሚኒ፣ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ፣ በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ተገኝተዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዓለምን ዓይን የሳበው የአፍሪካ ግዙፉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ በመሆኑ ብቻ አይደለም። ፕሮጀክቱ የአፍሪካን ህልሞች፣ ትብብር እና ቀጣናዊ ትስስር መልህቅ በመሆንም ጭምር ነው። የምረቃት ስነ ስርዓቱ ከአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ፣ አውሮፓ እና በተቀረው ዓለም በሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ዓለም አቀፍ ሽፋን አግኝቷል። ቢቢሲ በዘገባው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያንን በአንድነት ያቆመ የሀገር ኩራት ማሳያ መሆኑን ገልጾ የግድቡ ስኬት የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የዓመታት ጥረትና ድካም፣ በዜጎች የሀብት፣ የጉልበት እና የገንዘብ አስተዋፅኦ የተገኘ ውጤት መሆኑን አመልክቷል። ግድቡ ለሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን ህይወት እንደሚለውጥ ትልቅ ተስፋ እንደተጣለበትም አመልክቷል። ግድቡ የኢትዮጵያውያን ኩራት እና የቀጠናዊ ትብብር ማሳያ መሆኑን አበይት ጭብጡ አድርጎ ዘገባውን የሰራው ዶቼ ቬሌ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ የገንዘብ መዋጮ የተገነባው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች ታላቅ ስኬት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መግለጻቸውን አንስቷል። ግድቡ የተፋሰሱ ሀገራት የኢኮኖሚያዊ ውህደት እና ትብብር መሰረት መሆኑን የጠቀሰው የጀርመኑ መገናኛ ብዙሃን፤ ግድቡ፣ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሌላቸው ኢትዮጵያውን የኢነርጂ አቅርቦትን ከማረጋገጡ ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጿል። የተርኪዬ ዜና አገልግሎት አናዶሉ የሕዳሴ ግድቡን አስመልክቶ በሰራው ዘገባ የግድቡ ምረቃ ታሪካዊ ድል ሲል በዘገባው ላይ አስፍሯል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ከቅኝ ግዛት ዘመን ጀምሮ የነበረውን ኢፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀም የቀየረ መሆኑን ጠቅሶ ኢትዮጵያ የአፍሪካን ትልቁን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ እውን ማድረግ መቻሏን ጠቅሷል። አልጄዚራ የኢትዮጵያውያን የዘመናት ህልምን እውን ያደረገ ስኬት ነው ሲል በሰራው ዘገባ ያለምንም አይነት የውጭ እርዳታና ድጋፍ ፣በኢትዮጵያውያን የገንዘብ መዋጮና የቦንድ ግዢ መገንባቱ የግድቡን ስኬት የተለየ እንደሚያደርገው ገልጿል። በዜጎች ዘንድ ከፍተኛ የባለቤትነት ስሜትና የጋራ ኩራት የፈጠረ ፕሮጀክት መሆኑን ያመለከተው ዘገባው፤ ኢትዮጵያውያን የገጠማቸውን ፈተና አልፈው ያጠናቀቁት ግድብ የሀገራዊ አንድነት ማሳያ እና የትውልድ ቅብብሎሽ ውጤት እንደሆነም አንስቷል። ሲኤንን የሕዳሴው ግድብ ምረቃ ሀገራዊ ኩራት ምንጭ ሆኗል ያለ ሲሆን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትልቁን የኤሌክትሪክ ሀይል ማመነጫ ግድብ መሆኑንና ለሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ከማረጋገጡ ባለፈ የሀገር ኩራት ምንጭ መሆኑን ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የግድቡ አላማ ወንድም ሀገራትን መጉዳት ሳይሆን ለቀጣናው ብልጽግናን ማምጣት እንደሆነ መግለጻቸውንም በዘገባው ላይ አስፍሯል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መመረቅ ኢትዮጵያን የቀጠናው የኃይል ማዕከል ያደርጋታል ያለው ደግሞ አሶሲዬትድ ፕሬስ ነው። ኢትዮጵያ የአፍሪካን ትልቁን የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ስትመርቅ፣ ፕሮጀክቱ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በማሳደግ ለኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋፅኦ ከማድረጉ ባሻገር ጎረቤት ሀገራት ኃይል ለመግዛት የሚችሉበትን ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቅሷል። ታላቁ የሕዳሴው ግድብ መመረቅ ኢትዮጵያን የቀጣናው የኃይል ማዕከል ያደርጋታል ያለው ደግሞ አሶሲዬትድ ፕሬስ ነው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ትልቁን የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ስትመርቅ፣ ፕሮጀክቱ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ በማሳደግ ለኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋፅኦ ከማድረጉ ባሻገር ጎረቤት ሀገራት ከኢትዮጵያ ኃይል ለመግዛት እንደሚያስላቸው ነው በዘገባው ያመለከተው። የቻይናው ዢንዋ የሕዳሴው ግድብ ምረቃ የሀገራዊ ስኬት ማሳያ እንደሆነ ጠቅሶ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ትልቁ የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነውን ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በይፋ መርቃለች ሲል ገልጿል። በስነ ስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፕሮጀክቱ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንደሚያጠናክር፣ የተረጋጋ የኃይል አቅርቦትን እንደሚያረጋግጥና የቀጠናዊ የኃይል ትስስርን እንደሚያሳድግ መግለጻቸውን ዘግቧል። በምረቃው ላይ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች መገኘት የፕሮጀክቱን ቀጣናዊ ፋይዳ የሚያሳይ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የጎረቤቶቿን ጥቅም ሳይጎዳ በጋራ እድገት ላይ ያላትን ቁርጠኝነት በድጋሚ ማረጋገጣቸውን አውስቷል። አጠቃላይ ዘገባዎቹ የሕዳሴ ግድብ በቀጣናው፣ በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን የገዘፈ ተጽእኖ የሚያሳይ ነው። የሕዳሴ ግድብ ምርቃት ከመገናኛ ብዙሃን ባለፈ በዓለም ደረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦችን ትኩረት ስቧል። የአሜሪካ የቅድሞ ቅርጫት ኳስ ተጫዋች እና ታዋቂው የቲክቶክ የይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ የሕዳሴ ግድቡ ምርቃትን በአፍሪካ የተሰራ አዲስ ታሪክ ሲል ገልጾታል። ግድቡ በዓለም ላይ ከሚገኙ 20 ግዙፍ የኤሌትሪክ ማመንጫ ግድቦች አንዱ መሆኑንና ለወደፊት የኢትዮጵያን መጻኢ ጊዜ ብሩህ የሚያደርግ እንደሆነ ተናግሯል። ሕዳሴ የኢትዮጵያ ኢነርጂ ምርት በእጥፍ በመጨመር ሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ ያስችላል ብሏል። ግድቡ የሚያመነጨው ኃይል ለኢንዱስትሪ እና ማኑፋክቸሪንግ እድገት ትልቅ ሚና እንዳለው የገለጸው ዲላን የጎረቤት ሀገራት ኤሌክትሪክ በሽያጭ እንዲያገኙ ብር የሚከፍት እንደሆነም ጠቅሷል። ከ17 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ የቲክቶክ ተከታይ ባለው የዲላን ፔጅ ገጽ የተላለፈው መልዕክት ይህ ጽሁፍ እስከጠናከረተበት ሰዓት 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሰው ቪዲዮውን በመውደድ( ላይክ በማድረግ) ድጋፉን ገልጿል። በቲክቶክ ገጹ ላይ በጤና እና መዝናኛ ቪዲዮቹ የሚታወቀው የአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል የቀድሞ አባል ካጋን ዱንላፕ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት በኢትዮጵያ የኢነርጂ እና የመሰረተ ልማት ዘርፍ ትልቁ የሚባል ስኬት እንደሆነ ገልጿል። ግንባታው 14 ዓመታት የፈጀው ይህ ግዙፍ የሃይድሮ ፓወር ፕሮጀክት በራስ አቅም የተገነባና ይህም የብሄራዊ ጥረት ውጤትና የኢነርጂ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ መሆኑን አመልክቷል። ይህ የዱንላፕ ቪዲዮ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተከታይ ባለው የቲክቶክ ገጹ ላይ እስከ አሁን ከ165 ነጥብ 6 ሺህ በላይ ተመልካች አይቶታል። ኬንያዊቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ ብሪላ ናታሻ በቲክቶክ ገጿ ባስላለፈችው የቪዲዮ መልዕክት አፍሪካ በሕዳሴ ግድብ ታሪክ ሰራች ስትል ገልጻለች። የአፍሪካ የነጻነት ምድር የሆነችው ኢትዮጵያ ያለ ምንም የውጭ እርዳታ በኢትዮጵያውያን ገንዘብ እና ትልቅ መስዋዕትነት ማሳካቷን ተናግራለች። ኢትዮጵያ ግድቡን በራሷ እቅም መገንባቷ አፍሪካ መሰል ግዙፍ ፕሮጀክቶችን የማንንም እጅ ሳትጠብቅ መስራት እንደምትችል በግልጽ ለዓለም መልዕክት ያስተላለፈችበት ነው ብላለች። የግድቡ ምርቃት አፍሪካ በራሷ አቅም የራሷን ጉዳይ ለመፈጸም የወሰደችው ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጠቅሳ ምርቃቱ ድንቅ የሚባል ዜና እንደሆነ ተናግራለች። የቲክቶክ ገጿ ላይ 189 ሺህ 500 ተከታይ ያላት ናታሻ ግድቡን አስመለክቶ ያስተላለፈችው መልዕክት እስከ አሁን ባለው መረጃ 33 ሺህ 800 ሰዎች በመውደድ አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ከዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እና ተጽኦ ፈጣሪ ግለሰቦች ሀሳብ ወጣ ስንል የግድቡ ምርቃት የአፍሪካ የአይበገሬነት እና የጽናት ምልክት፣ ራስን የመቻል እና የቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ትብብር መገለጫ ሆኖ የታየበት ነው። የምስራቅ አፍሪካ መሪዎች በምርቃቱ ላይ መገኘት የአፍሪካ ፕሮጀክት የሆነው ሕዳሴ ግድብ ኢኮኖሚን በመቀየር፣ የኢነርጂ ዋስትናና ደህንነት በማረጋገጥ እና ድንበር ተሻጋሪ የዲፕሎማሲ ትስስር መጋመጃ መሆኑም ታይቶበታል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካ የራሷን እጣ ፈንታ በራሷ የመወሰን አቅም እንዳላት የሚያሳይ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በግድቡ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ገልጸዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ትልቅ ታሪካዊ አንድምታ አለው ያሉ ሲሆን አፍሪካውያን የራሳቸውን የብልጽግና መሻት በራሳቸው ማካሳት እንደሚችሉም የሚያመላክት መሆኑን አመልክተዋል። የሕዳሴ ግድብ ከብሄራዊ ፕሮጀክትነት ባለፈ የፓን አፍሪካ አቅምን በተግባር ያሳየና የአፍሪካ መር መሰረተ ልማት ግንባታ መገለጫ ነው ያሉት ሩቶ ግድቡ በቀጣናው ለሰላም እና ብልጽግና ያለንን የጋራ ህልም ማሳካት በእጃችን ያለ ጉዳይ መሆኑን የሚያሳይ ነው ብለዋል። በግድቡ ምርቃት ላይ የተገኙት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አህጉራዊ ትብብርና ግንኙነትን የሚያጠናክር የወንድማማችነት ምልክት እንደሆነ ተናግረዋል። የላይኛውና የታችኛው ተፋሰሱ ሀገራት መበልጸግ የሚችሉት በጋራ እንደ አንድ ማህበረሰብ በመስራት መሆኑን ገልጸው፤ ውሃና ሌሎች ተፈጥሯዊ ሀብቶች በድንበር የተወሰኑ ሳይሆኑ የወደፊት እጣ ፈንታችንን የሚያስተሳስሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል። የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት የሕዳሴ ግድቡ መመረቅ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የኩራት ቀን ነው ያሉ ሲሆን ግድቡ የኃይል ፍላጎትን ከማሳካት ባለፈ ለልጆቻችን የምንመኘውን የበለጸገ ሀገርና አህጉር ለማስረከብ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን ፕሮጀክት ነው ያሉት ደግሞ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ናቸው። ግድቡ የዓለምን ሕዝብ ያስደነቀ የአፍሪካ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሐሙድ አሊ ዩሱፍ ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ገንብታ ለምረቃ ያበቃችው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከሀገሬው አልፎ ለጎረቤት ሀገራት ብርሃን ነው ሲሉ ገልጸዋል። የዚህ ፕሮጀክት ስኬት ከአኅጉራዊ አጀንዳዎች ጋር የሚጣጣም መሆኑን በመጥቀስ፤ ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ በመገንባት ኢትዮጵውያንን እና ቀጣናውን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በራስ አቅም የገነባችው በመሆኑም፤ የሚደነቅና ለአኅጉራችን መነሳሳትን የሚቸር ተግባር ነው ብለዋል። 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት የሚያመነጨው ሕዳሴ በየቤቱ ብርሃንን በመስጠት፣ ለኢንዱስትሪዎች አለኝታ በመሆንና ከምስራቅ አፍሪካ ባሻገር እድገትን ለማሳለጥ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። የሕዳሴ ግድብ ከዲፕሎማሲ አኳያ የአፍሪካ መር ስኬትን በግልጽ የሚያመላክት ነው። ግድቡ በኢትዮጵያውያን የራስ አቅም መገንባቱ አፍሪካ የራሷን የልማት መንገድ በራሷ የመወሰን አቅም እንዳላት የሚያመላክትም ነው። ግድቡ ኢትዮጵያ እና የተፋሰሱ ሀገራት በትብብርና በውይይት አማራጭ የውሃ ሀብትን ለጋራ ልማት እና እድገት መጠቀም እንደሚቻል በግልጽ ያሳዩበት ነው። የዓለም አቀፍ መገናኘ ብዙሃንን ከፍተኛ ትኩረት የሳበው የሕዳሴ ግድብ ምርቃት የዜና ዘገባዎች ግድቡ የክፍፍል ሳይሆን የአፍሪካ አንድነት እና ለውጥ ተስፋ መሆኑ ተንጸባርቋል። ፍሪካ በአጀንዳ 2063 ሁሉን አቀፍ እድገት እና ዘላቂ ልማትን እውን ለማድረግ እየተጋች ይገኛል። ሕዳሴ ግድብ ከዚህ አህጉራዊ ማዕቀፍ አንጻር ትልቅ አህጉራዊ ስኬት ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግድቡ መብራትን የሚያበራ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን የመልማት አቅም የሚያስመነድግ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። ዓለም የሕዳሴ ግድብ የራስን መቻል፣ የአይበገሬነት፣ የለውጥ እና መጻኢ ጊዜን ብሩህ የማድረግ ተምሳሌት እንደሆነ በግልጽ መስክሯል።
ከ500 በላይ ሥራዎችን የሚያሳልጠው ጉበት …
Sep 1, 2025 955
ጉበት ከ500 በላይ ሥራዎችን የሚያከናውን ዋነኛ እና ሁለገብ የሰውነታችን አካል ነው ይላሉ በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የጨጓራ፣ አንጀት እና ጉበት ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር አብዲ ባቲ። የጉበት ተግባራት በአራት ዐቢይ ክፍሎች እንደሚከፈሉም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። 👉 የመጀመሪያው ተግባሩ፤ ጎጂ ንጥረ ነገሮችን ከደም ውስጥ ማጽዳት፣ ቆሻሻ ምርቶችን ማስወገድ፣ የመድኃኒቶችን ሜታቦሊዝም ማከናወን፣ ከምንበላው፣ ከምንጠጣው እና ከምንተነፍሰው ሁሉ መርዞችን ማስወገድ ነው ይላሉ። 👉 እንዲሁም ሁለተኛው ተግባሩ፤ ቫይታሚኖችን፣ ማዕድናትን እና ኃይልን ማከማቸት መሆኑን ገልጸው፤ ለሰውነታችን ማበረታቻ ኃይል በሚያስፈልግበት ጊዜ ዝግጁ ማድረግ ነው ብለዋል። 👉 ሦስተኛው ተግባር ደግሞ፤ ለደም መርጋት እና ኢንፌክሽኖችን ለመዋጋት ፕሮቲኖችን ማመንጨት መሆኑን ያስረዳሉ። 👉 አራተኛው ተግባሩን ሲያብራሩም፤ ‘Bile’ የሚባል ንጥረ ነገር በማምረት ከሚወዷቸው (ከሚመገቧቸው) ምግቦች ውስጥ የሚገኘውን ስብ እንዲፈጭ ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል። ጉበትን ለህመም የሚያጋልጡ መንስኤዎች ምንድን ናቸው? • እንደ ዶክተር አብዲ ገለጻ፤ ጉበት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ያለው ወሳኝ የሰውነት አካል እንደመሆኑ ለብዙ አደጋዎች ይጋለጣል። ከነዚህ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ ናቸው ብለዋል። 👉 እንደ ሄፓታይተስ ቢ እና ሲ ባሉ ቫይረሶች በደም፣ በመርፌ ወይም ወሊድ ወቅት የሚተላለፉ፤ 👉 ከመጠን በላይ አልኮል መጠቀም፤ 👉 ከመጠን በላይ መወፈር ፤ 👉 የስኳር በሽታ፤ 👉 ከእፅዋት እና የተለያዩ እህሎች (ለምሳሌ ከማሽላ እና በቆሎ) ውስጥ የሚገኙ እንደ አፍላቶክሲን ያሉ መርዛማ ንጥረ ነገሮች ይገኙበታል ብለዋል። 👉 በተጨማሪም ከ40 ዓመት በላይ መሆን፣ በቤተሰብ የሚተላለፉ የጉበት በሽታዎች መኖር፣ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እና አደገኛ ልማዶች ለጉበት በሽታ ከሚያጋልጡ መንስዔዎች መካከል ናቸው ይላሉ። ከእነዚህ አጋላጭ መንስኤዎች አብዛኛዎቹ ሊወገዱ የሚችሉ እንዲሁም ቀድመን በማወቅ እና በመጠንቀቅ መከላከል የሚቻሉ ናቸው ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። ጉበትን በቀላል እና ጤናማ በሆኑ ልምዶች እንዴት ማበረታታት ይቻላል? • በየዕለቱ በቂ ንጹህ ውኃ በመጠጣት፤ • ጤናማ አመጋገብ በመከተል (እንደ ፍራፍሬ፣ አትክልት፣ ጤፍ፣ ባቄላ እና ዓሣ በመመገብ)፤ • ከመጠን በላይ ስብን እና ስኳርን በመቀነስ፤ • አካላዊ እንቅስቃሴን በማዘውተር፤ • አልኮልን በመገደብ ወይም በጭራሽ ባለመጠቀም፤ • የሄፓታይተስ ክትባት በመውሰድ፤ • ያልተረጋገጡ እፅዋትን ከመጠቀም በመቆጠብ፤ • መድኃኒት ከመውሰድ በፊት የጤና ባለሙያ በማማከር እንዲሁም የግል እና የምግብ ንጽህናን በመጠበቅ የጉበትን ጤንነት መጠበቅ ይቻላል ብለዋል ዶክተር አብዲ። ሕክምናውን በተመለከተ o ዶክተር አብዲ እንዳሉት፤ አብዛኛዎቹ የጉበት በሽታዎች ሊታከሙ ይችላሉ፤ በጊዜ ከተደረሰም መቆጣጠር እና መዳን ይችላሉ። o ለሄፓታይተስ ቢ/ሲ ፀረ-ቫይረስ መድኃኒቶች ሕክምና መከታተል፤ o አልኮል መጠጣት በማቆም ጉበት በፍጥነት እንዲያገግም ማገዝ፤ o ለሰባ ጉበት፣ ለስኳር በሽታ እና ለኮሌስትሮል መብዛት በመድኃኒት ማከም፤ o አመጋገብን ማስተካከል፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፤ o የከፋ ደረጃ ላይ የደረሰ ከሆነ እንደደረጃው የተለያዩ ሕክምናዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ እስከ ንቅለ ተከላ ድረስ ሊታከም ይችላል ብለዋል። ጉበት በዓለም አቀፍ ደረጃ…. 👉 በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ 2 ቢሊየን የሚጠጉ ሰዎች እንደ ሄፓታይተስ ቢ እና ሲ ያሉ የጉበት ህመሞች ተጋላጭ ናቸው። ለዚህም ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣት፣ ውፍረት እና የስኳር በሽታ በሰፊው በዓለም አቀፍ ደረጃ ብዙዎችን ተጋላጭ ያደርጋሉ ነው ያሉት። 👉 በአፍሪካ ውስጥ ወደ 80 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች ለሄፓታይተስ ቢ በሽታ ተጋላጭነት ውስጥ ይኖራሉ። ከዚህ ውስጥ 60 በመቶው የሚሆነው በክትባት ውስንነት፣ በጤና አጠባበቅ ተደራሽነት እና በአፍላቶክሲን የተበከሉ (እንደ በቆሎ እና ማሽላ ባሉ) ሰብሎች ምክንያት ለአደጋ ተጋላጭ ነው ብለዋል። 👉 በኢትዮጵያም እስከ 7 በመቶ ያህሉ ሕዝብ ለሄፓታይተስ ቢ ተጋላጭ መሆኑን ነው ያመላከቱት። ለዚህም አልኮል አላግባብ መጠቀም፣ ጫት መጠቀም እና የስኳር በሽታ መጨመር ለብዙዎች በተለይም ከ40 ዓመት በላይ ለሆኑ ወንዶች ተጋላጭነትን እንደሚጨምር አስገንዝበዋል። 👉 በአጠቃላይ ክትባት በመውሰድ፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ በመከተል፣ ጤናማ አመጋገብ በማዘውተር ብሎም በወቅቱ በመታከም ተጋላጭነትን በመቀነስ የጉበት ጤንነትን መጠበቅ ይገባል ሲሉ መክረዋል።
አስም-የበርካቶች ሰቀቀን …
Aug 28, 2025 1001
በወቅትና የአየር ሁኔታ ሳይገደብ የበርካቶች ስቃይ የሆነውን አስም እንዴት ማከም ይቻላል…? የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • አስም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ፍጹም ገለጻ፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም አስም ይባላል። • የአስም ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው? የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ በአብዛኛው ምልክቶቹ በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ ገልጸዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸው፤ ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር) ብናኝ፣ የእንስሳት ፍግ ሽታዎች አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ያስረዳሉ። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑን አስረድተዋል። • ለአስም ህመም አጋላጭ ወይም ለህመሙ መባባስ መንስኤዎቹ ምንድን ናቸው? አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የአየር ብክለት፣ ጭስ)፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ዶክተር ፍፁም ገልጸዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ በቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ ወቅት ሙቀት የሚሰጡ ልብሶችን መልበስ፤ ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። • ሕክምናውስ ምንድን ነው? የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የአየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል።
አሸንዳ- የፍቅርና የሰላም አጀንዳ
Aug 23, 2025 1179
በአማረ ኢታይ የሴቶች በተለይም የልጃገረዶች በዓል መሆኑ የሚነገርለት የአሸንዳ በዓል ለማክበር አመቱ እስከሚደርስ ድረስ በጉጉትና በናፍቆት ይጠበቃል። አሸንዳ ይዋቡበታል፣ ቁንጅና ጎልቶ ይወጣበታል፣ ልጃገረዶችና ሴቶች ተሰባስበው የሚያዜሙበት፣ በስጦታ ጭምር የሚታጀብ ልዩ እና ውብ የአደባባይ በዓል ነው። የአሸንዳ በዓል ሲቃረብ በተለይ ልጃገረዶች ቀደም ብለው የመዋቢያ ጌጣጌጦችንና አልባሳትን አዘጋጅተው የበዓሉን መድረስ ይጠባበቃሉ። እለቱም ሲደርስ በተለየ ሁኔታ ተውበውና ደምቀው ከበሮ ይዘውና በጣእመ ዜማ ታጅበው ወደ አደባባይ በመውጣት ያከብሩታል። በዚህም መሰረት ትግራይ የአሸንዳ በዓል በየዓመቱ ከነሃሴ 16 ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በደማቅ ስነ ስርአት ይከበራል። እለቱ የልጃገረዶች የነፃነት ቀንም በመሆኑ የቤተሰብ፣ የዘመድ አዝማድ ቁጣ እና ይህን አድርጊ ይህን አታድርጊ የሚል ትእዛዝ እና ጫና አይኖርም። በመሆኑም አሸንዳ - የነፃነት፣ የፍቅርና የሰላም አጀንዳ ያነገበ በመሆኑ ከልጅ እስከ አዋቂ በየአመቱ በጉጉት የሚጠበቅ ደማቅ በዓል ነው። የአሸንዳ ልጆች ከበዓሉ ዋዜማ ጅማሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ በየሰፈራቸው በቡድን በቡድን ተሰባስበው የሚጫወቱበት በመሆኑም የህብረት፣ የፍቅር፣ የሰላምና የአብሮነት ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። ወላጆቻቸው አነስተኛ ገቢ ያላቸው ልጃገረዶችም ከእኩዮቻቸው፣ ከዘመድ አዝማድ እና ከጎረቤቶቻቸው የመዋቢያ ጌጣጌጦችን፣ አልባሳትና ሌሎች ቁሶችን ወስደው በዓሉን በደስታ የሚያሳልፉ ይሆናል። በዚህም መሰረት በዓሉ የመረዳዳት፣ የትብብርና ችግርን በመተጋገዝ ማለፍ እንደሚቻል የሚያመላክት ልዩ በዓል ነው። በዚሁ መሰረት የ2017 ዓ.ም የአሸንዳ በዓል በደማቅ ስነ ስርአት በመከበር ላይ ይገኛል። የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች፣ በርካታ ቱሪስቶች ልጃገረዶችና ሌሎችም የበዓሉ ታዳሚዎች በተገኙበት በመከበር ላይ ነው። በክብር እንግድነት በመገኘት ንግግር ያደረጉት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፤ ኢትዮጵያ በርካታ ውብ የሆኑ መገለጫዎች ያሏት ሀገር በመሆኗ አጉልተንና ለዓለም አስተዋውቀን የውበታችን ማሳያ እና የሃብት ምንጭ ጭምር ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል። የአሸንዳ በዓልን እሴት በመጠበቅ ለትውልድ ለማስተላለፍ ተቀናጅተን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የሚከበሩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን በማክበር ጠብቆ ማዝለቁ እንዳለ ሆኖ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን የማልማትና ታሪካዊ ቅርሶችን መጠበቅም ትኩረታችን ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። በመጨረሻም የአሸንዳ በዓልን በድምቀት እያከበረ ለሚገኘው ለመላው የትግራይን ህዝብ በተለይም ለልጃገረዶች የሰላምና የፍቅር በዓል እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል። "የአሸንዳ በዓልን ማስዋብና ማድመቅ ለሰላምና ለአንድነት ያለንን መልካም ፍላጎትና ምኞት ማሳያ ነው። ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና እንዲለማ እንሰራለን።" በማለት መልእክታቸውን ያጋሩት ደግሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ናቸው። በጊዜያዊ አስተዳደሩ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አፅበሃ ገብረእግዛብሄር በበኩላቸው፣ ባህላዊ ይዘት ያለው የአሸንዳ በዓል ሳይበረዝ ትውፊቱን ጠብቆ እንዲቀጥል የክልልና የፌዴራል መንግስታት በጋራ እንሰራለን ብለዋል። በመቀሌ ከተማ እየተከበረ ባለው የአሸንዳ በዓል ከባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ በተጨማሪ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እና ሌሎችም ታድመዋል። አሸንዳ - የነፃነት፣ የፍቅርና የሰላም አጀንዳ ሆኖ መከበሩንም ቀጥሏል።
ትንታኔዎች
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 803
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 1697
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 1911
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 5094
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 5106
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 3918
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 5431
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል። በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል። የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
መጣጥፍ
የሀመሯ እናት- የደስታ እንባ
Sep 11, 2025 623
የሀመሯ እናት- የደስታ እንባ በጣፋጩ ሰለሞን (ከጂንካ) በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኘው ሐመር ወረዳ የሐመር ብሔረሰብ ዘመን በተሻገሩ ባህላዊ ሥርዓቶች ይታወቃል። በዚህ አካባቢ ከሚዘወተሩትና በብዛት ከሚታወቁት ባህላዊ ሥርዓቶች መካከል “ኢቫንጋዲ እና ኡኩሊ” የተባሉ ባህላዊ ጨዋታዎች ይጠቀሳሉ። “ኡኩሊ”በሐመሮች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ባህላዊ ጨዋታ ሲሆን ለአቅመ አዳም የደረሰና ከብት ለመዝለል ዝግጁ የሆነ የሐመር ወጣት የሚጠራበት የማዕረግ ስም ነው፡፡ “ኡኩሊ” ከብት በሚዘለልበት ዕለት ሥርዓቱ በሚፈጸምበት ሥፍራ ላይ በቅርብም ይሁን በሩቅ ያሉ የወጣቱ ዘመዶች ተጠርተው የሚከናወን ባህላዊ ሥርዓት መሆኑ ይታወቃል። “ኢቫንጋዲ” ደግሞ በሐመሮች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ባህላዊ ጭፈራ ሲሆን ትርጉሙም “ኢቫን” ማለት “ ማታ” ሲሆን “ጋዲ” ማለት ደግሞ “ጭፈራ” ማለት መሆኑ ይነገራል። ኢቫንጋዲ በአዝመራና በደስታ ወቅት በሥራ የደከመን አእምሮና አካል ለማዝናናት ሲባል የሚከናወንና የሀመር ወጣቶች በጉጉት የሚጠብቁት ባህላዊ ጭፈራ ነው። በዚህ ባህላዊ ጨዋታ ላይ የሐመር ወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች አምረውና ተውበው በጨረቃ ብርሃን ይጨፍራሉ። የኢቫንጋዲ ጭፈራ በሶስት ቀን አንድ ጊዜ በሐመር መንደሮች በምሽት ከጨረቃ ድምቀት ጋር አብሮ ይደምቃል። “በጨረቃ ብርሃን አየኋት በማታ ኢቫንጋዲው ቦታ” የተባለላቸው የሃመር ውብ ልጃገረዶችም ከጨረቃ ብርሃን ጋር ደምቀው የሚታዩበት ዕለት ይሆናል። በወጣትነታቸው በዚሁ ባህላዊ ሥርዓት ያለፉት የሀመሯ እናት- ወይዘሮ ባሎ ኡርጎ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ እናት ናቸው። በሐመር ወረዳ ዲመካ ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ ባሎ፤ በደሳሳ ጎጇቸው ሲያገኙ በልተው ሲያጡ ደግሞ ኩርምት ብለው ያሳለፉባቸው ጊዜያት እንዳሉ ያስታውሳሉ። በደሳሳ ጎጆ እየኖሩ ዝናብ ሲመጣ የጎርፍ፣ ብርድና ዶፉ ስጋት ላይ ጥሏቸው እንደኖሩ ያነሳሉ፤ በበጋ ወራት ደግሞ የሚነፍሰው ነፋስና ሀሩሩ ጸሃይ ይፈትናቸው እንደነበር ይናገራሉ። ከእለታት አንድ ቀን ወጣቶችና ጎልማሶች ጭምር ሰብሰብ ብለው መጥተው “ቤትዎን በነፃ ልናድስልዎት ነው ሲሉኝ አላመንኳቸውም ይላሉ። የእውነታችሁን ነው አልኳቸው? አዎን ቤትዎን አፍርሰን ልንሰራልዎት ነው” ብለው አረጋገጡልኝ በማለት ሁኔታውን በደስታ እንባ ታጅበው ያስታውሳሉ። በተባለው መሰረትም በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የቤታቸው እድሳት ተጀምሯል። የኢዜአ ሪፖርተር በስፍራው ተገኝቶ ወይዘሮ ባሎን ባነጋገራቸው ወቅት “ሰው በሚያስፈልገኝ ጊዜ ሰዎች ሁነው የተገኙ ወገኖቼ ችግሬን ለመፍታት በአካል ተገኝተዋል፤ በጣም ደስ ብሎኛል፤ የመኖርን ተስፋ እንድሰንቅ አድርገውኛል በማለት ደስታቸውን በእንባቸው ጭምር ታጅበው ገልጸዋል። የሀመሯ እናት ቤታቸው በፍጥነት ታድሶ የሚረከቡ፣ በቀጣይም አስፈላጊው እገዛና ድጋፍ የሚደረግላቸው መሆኑን የቤቱን እድሳት ያስጀመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኤካል ነትር አረጋግጠዋል። እንደ ወይዘሮ ባሎ፤ ያሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችን የማገዝና የመደገፍ ሃላፊነት አለብን ያሉት ሃላፊው፤ የመረዳዳትና የመተጋገዝ ባህል ጎልቶ እንዲቀጥል ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል። የቢሮው የማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች ለወገኖቻቸውያላቸውን አለኝታነት በተግባር በማሳየታቸውም አመስግነዋል። የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ፤ የዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ ተቋማት፣ግለሰቦች፣ወጣቶችና አዛውንቶች ሳይቀር የተሳተፉበት እና የበርካቶችን ችግር መፍታት የተቻለበት መሆኑን ተናግረዋል። የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች የወይዘሮ ባሎን ቤት ለማደስ በመምጣታቸው አመስግነው፤ ለሌሎች ተቋማትም አርአያ የሚሆን የመልካምነት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ በተያዘው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ቤቶችን ጨምሮ የዞኑን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም በዞኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችን የመደገፍና ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን በስፋት የማከናወን ተግባር በተጠናከረ መለኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የአባይ የቁጭትና የወቀሳ ጊዜ አበቃ!
Sep 9, 2025 554
የአባይ የቁጭትና የወቀሳ ጊዜ አበቃ! (በቀደሰ ተክሌ - ከሚዛን አማን) አኩርፎ ከቤት ቢወጣ ለመመለስ ሸምጋይ አጥቶ በሰው ሀገር ተንከራታች ልጓም አልባ ሆኖ የኖረው አባይ ከኢትዮጵያ አፈር፣ ማእድናትና ሌሎችንም ሃብቶች ጠርጎ በመውሰድ ለዘመናት ሲፈስ ኖሯል። ከኢትዮጵያ እምብርት በመነሳት አገራትን አቆራርጦ የሚያልፈው፣ የዓለማችን ታላቁ ወንዝ አባይ በጋና ክረምት ሳይል በመፍሰስ የብዙዎች የህይወት ምንጭ ሆኖ አሁንም ፍሰቱን ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ልጅ የኢትዮጵያውያን አብሮነት ምሰሦ - የወንዞች ንጉሥ ታላቁ አባይ! አሁን ልጓም ተበጅቶለት በፍትሃዊነት ሁሉንም ለመጥቀም ተዘጋጅቶ የማይነጥፈው ጅረት ዘላለማዊ የመፍሰስ ሂደቱ እንደቀጠለ ነው። ኢትዮጵያውያን አመሉ ለከፋ፤ እሺ በጀ አልል ብሎ በእንቢታ ልቡን ባጸና ልጅ አብዝተው ያዝናሉ። የሀዘናቸው ጥግም በሕይወት ሳለ የሞተ ያክል በእንጉርጉሮ ሙሾ ያወርዱለታል። አባይም ይህ እጣ ፈንታ ገጥሞት "አመፀኛ ውሃ" ተብሎ በወቀሳ ተዚሞለታል። ለኢትዮጵያ ለዘመናት ሳይታዘዝ የኖረው አባይ የአዛዥ እጦት እንጂ በእምቢታ አልነበረም። በዚህ ውጣ በዚህ ግባ ባይ አጥቶ ቦዘነ። በዚህም ተራራውን እየሸሸ ቁልቁል እየተምዘገዘገ፣ ሲሻ እየጬሰ ቁልቁል ወርዶ ከዐለት ጋር እየተጋጨ መዳረሻውንና ማደሪያውን ይናፍቃል። በዚህም ቤቱን ረሳ። ወላጆቹን ትቶ ባእዳንን ብቻ ጦረ፣ ፊቱን በፍጹም ወደ ኋላ እንዳይመልስ እንደ ሎጥና ቤተሰቦቹ ተገዘተ። አባይ የባእዳንን ግዝት ከተፈጥሮ ጋር አስተባብሮ በመጠበቅ ሀገሩን ለቆ ከመውጣት ውጭ ቢደክመው የማረፍ፥ ቢመቸው የማልማት መብት ሊያገኝ አልቻለም። ይህ በኢትዮጵያ ልብ ውስጥ ቁጭት ፈጥሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ ለታላቅ ልጇ ማረፊያ ሠርታ ጎጆ ልታወጣ ቋመጠች። ፈተናው በዛ የፖለቲካ መልክ ይዞም አቅሟን ተፈታተነ። ስደተኛው አባይን ስላሳረፉት እርሱም ስለመገባቸው የግል ሀብት አድርገው የቆጠሩት የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጫና ፈጥረው የሀሳብ ጽንሱን ከታሪካዊና ቀጣናዊ ጠላቶች ጋር እየተባበሩ አቋረጡት። አባይን ገድቦ የመጠቀም የዘመናቱ የኢትዮጵያ መሪዎች ጉጉቱ ህልም ሆኖ ሐዘኑ ከነ ቁጭቱ ቀጠለ። እንጉርጉሮ ወቀሳ በበዛባቸው ስንኞች ቋጥሮ መዜሙን ቀጠለ። የኢትዮጵያ ዐይኖች ጀግንነት በአባይ ሲሸበብ ማየት አንገሸገሻቸው። የበይ ተመልካች መሆንና ከጓሯቸው ሞፈር አስቆርጦ መራብ አመማቸው። ኢትዮጵያዊነት ከዘመን ዘመን የማይነጥፍ፥ ልብ ለልብ የተሳሰረ ትውልድ ማንነት ማሳያ ሐውልት ነው። ትላንት ዛሬን እያቃና ነገን የሚገነባበት ሀገራዊ ራእይ ያላቸው መሪዎች ትስስር በአባይ ሲንጸባረቅ ይስተዋላል። ከ1929 እስከ 1950ቹ ያለው የአባይ ፖለቲካ ጉዳይ በብዙ ድርድሮችና ስምምነቶች ታጀበ። የጫና ፈተናው አየለና ገንብቶ የመጠቀም ጥንስስን ለቀጣይ ትውልድ እንዲሸጋገር አደረገ። ያኔ ነገን የተመለከተ ዐይን "ልጆቻችን ይሠሩታል" የሚል ቃል ሰጠና ኢትዮጵያ ልጆቿን በተስፋ ተጠባበቀች። ዘመን አለፈ ትውልድ ተተካ ልጆችም ተወለዱና የተስፋ ቀጠሮ ደረሰ ወርሃ መጋቢት 2003 ዓ/ም። በዚህ ቀን የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዜና በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ተበሰረ። ኢትዮጵያ እልል አለች፤ "እንጉርጉሮ ይብቃ" ተባለ በዜማ በዝማሬ አባይ ተሞገሰ። የአባይ የወቀሳ ጊዜ ተጠናቀቀ- የቁጭት ጊዜ አብቅቶ የስኬትና ማንሰራራት ጊዜ መጣ። ለግድቡ የ14 ዓመታት የግንባታ ሂደት ከአንድ ብር ጀምሮ አስተዋጽኦ ያደረጉ፣ በእውቀትና በጉልበት የተጉ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የደስታ ቀንም እውን ሆነ። በጉባ ሰማይ ስር አዲስ ክስተት፣ አዲስ ምዕራፍ፣ አዲስ ስም ተተከለ። አባይ ከሚል ነጠላ ስም ወደ "ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ" ተሻገረ። የድግቡ ሃይቅም "ንጋት" የሚል መጠሪያ ወጥቶለት ለኢትዮጵያ የንጋት ጸሃይ እየወጣች መሆኑን ለሁላችንም ብስራት ሆነ። "እንኳንም ጀመርን፣ እንኳንም በር ተከተፈተልን" እንጂ ያሉት ልበ ኩሩና ክንደ ብርቱ ኢትዮጵያውያን ጫናዎችን በአይበገሬነት መንፈስ ድባቅ እየመቱ ጉዞ ወደ ፊት ቀጠሉ። ወደ ተግባር ገብተው "ሕይወታችንንም ቢሆን ለአባይ አንሰስትም" አሉ። ግድቡን እንሠራለን ብለው የጀመሩት ኢትዮጵያውያን ናቸው። ከነ አባባላቸው "የነብር ጭራን አይያዙ፥ ከያዙም አይለቁ" ነውና ሥራውን ስለጀመሩት የአባይ ግድብ ጉዳይ ቀዳሚ አጀንዳቸውና ደም ስራቸው ሆኖ ቀጠለ። እንደ ዐይን ብሌናቸው ያዩ፣ ይጠብቁት እና ይሳሱለት ጀመር። የአልሸነፍ ባይነት ወኔን ከጀግንነት ጋር አጣምረው የያዙ ኢትዮጵያውያን የጠላት ነቀፋና ፕሮጀክቱን የማኮላሸት ሴራን እንደ ድር አብረው ተከላከሉ። የ"እንችላለን" ትርክትን በተግባር ነፍስ እየዘሩ እጅ ለእጅ ተያይዘው ጉዟቸውን ከሕዳሴ ጋር ቀጠሉ። በጉባ ምድር ላይ የአንድነታቸውን ቋሚ ሐውልትም ተከሉ። ኢትዮጵያውን ከአድዋ ጦርነት ወዲህ የአንድ ቃል ተናጋሪ የአንድ ልብ መካሪ ሆነው የተከሰቱበትና በአንድ የተመሙበት ትልቁ የታሪክ አሻራ አባይ በሕዳሴ ሆነ። የተማሪ ቦርሳ፣ የእናቶች መቀነት፣ የአረጋውያን የጡረታ ደብተር፣ የአርሶ አደሮች ጎተራ፣ የአርብቶ አደሮች በረት፣ የመንግሥት ሠራተኛው ፔሮል፣ የነጋዴው ኪስ እና የዳያስፖራ ዋሌት ሳይቀር በአባይ ላይ አሻራ አለው። የሕዳሴው ግድብ ውዝግብ ኢትዮጵያ ራሷን በዓለም መድረክ ከፍ አድርጋ ያሳየችበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የደረሰውን ውሃ አይሞላ ክስ በብስለት መክታ እውነትን ለዓለም ሕዝብ አስገንዝባለች። በዚህም የዓለም አቀፍ ሕግ አዋቂነቷንና አክባሪነቷን፣ የጋራ ተጠቃሚነት ፍላጎቷንና ለሰላም ያላትን አቋም ቁልጭ አድርጋ አረጋግጣለች። ድርድሮችን በድል የሚቋጩ ልጆቿ ደግሞ ኢትዮጵያውያን በሁሉም ዘርፍ ብቁ የመሆናቸው ነጸብራቅ ሆነው ተከሰቱ። ዘርፈ ብዙ የዲፕሎማሲ ሥራው ከማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ እስከ ጉምቱ አምባሳደሮች በተናበበ መልኩ ብቅ ብሎ አጀብ አስብሏል። ድርድሩ በመስመሩ፣ የዲፕሎማሲ ሥራው በሜዳው ፖለቲካ እና ሌላው የሀገር ጉዳይ በየፈርጁ እየቀጠለ የሕዳሴው ግድብም ለደቂቃ እንኳ ሳይቆም ይሠራ ነበር። ይህ የመብቃት፣ የማደግ፣ በጥበብ የመበልጸግ፣ በሀሳብና አቅም የመብሰል ሀገራዊ ማሳያ ነው። ለብዙ የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚሆን አሻጋሪ የተግባር ልምምድ መሆኑም አያሻማም። ለዚህ ግድብ ስኬት ደግሞ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን መሪ ሆነው ብቅ ያሉትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶር) ማንሳት ግድ ይላል። አዛዥ አጥቶ ቦዝኖ የነበረውን ጊዜ ለመካስ ና ብሎ የሚጣራውን አዛዥ "አቤት" ብሎ ትዕዛዝ ለመቀበል አባይ አላቅማማም። አሁን በሙሉ ልቡ ወደ ጫጉላ ቤቱ ገብቷል። የመስከረሙ ሙሽራ የቤት ሀብት ዘርፎ ለባዕድ አሳልፎ ከመስጠት ተቆጠበ። የበረሃው ሀሩር ሳይመታው በሀገሩ እፎይ ብሎ ብርሃንም ምግብም፣ ሀብትም ክብርም መሆን ጀመረና የኢትዮጵያን ክብር ዳግም ከፍ አደረገ። ሰው ተፈጥሮን ሲያዝ እሺ ይላል፥ ዝም ካሉት በራሱ ፍላጎት ይሔዳል። ይህ ተፈጥሯዊ የአባይ ግብር ተቀይሮ በሰዎች መታዘዝ ጀመረ። አፈርና ውሃ ማስቀረት ብቻ ሳይሆን ግዙፍ የብርሃን ምንጭ ሆኖ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ብርሃን መሆን ጀምሯል። በሕዳሴ ግድብ ታዞ ፊቱን ወደ ልማት ሥራ ያዞረው አባይ ያለፈውን ለመካስ ብዙ ጸጋዎችን ይዞ ተከሰቷል። የዓሳ ምርት፣ ግዙፍ ሀይቅ ከደሴቶች ጋር አንጣሎ በመያዝ የኢኮ ቱሪዝም ዘርፍ መሪ ሊሆን ቆርጦ ተነስቷል። አብሮ የመልማት የኢትዮጵያ ጽኑ ፍላጎት በወለደው እሳቤ ህዳሴ ግድብ የጎረቤት አገራት ሃብት ጭምር በመሆን ለማገልገል ተዘጋጅቷል። አባይ ሆይ ስምህ ከወቀሳ ወጥቶ በሙገሳ ስለተተካ እንኳን ደስ አለህ! እናቴ ሆይ የተፈታው መቀነትሽ ሀይል ስላመነጨ ለልጆችሽ ሀብት አውርሰሻልና ደስ ይበልሽ። ሀገሬ የብርሃን ዘመን ስለፈነጠቀብሽ እንኳን ደስ አለሽ! ሰላምና ፍቅር ለሁላችን ይሁን።