ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ኮሚሽኑ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስኬት ከመገናኛ ብዙኃን አመራር አባላትና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር ተወያየ
Jun 20, 2026 200
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን ለማሳካት የሚያስችል ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር መሀሙድ ድሪር፣ ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም እና ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) መገናኛ ብዙኃን እስካሁን ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነዋል። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር እንደገለጹት፤ መገናኛ ብዙኃን ለህብረተሰቡ ትክክለኛ መረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።   በተጨማሪም የሀገራዊ ምክክሩን ትክክለኛ ገጽታ ለዓለም ማኅበረሰብ ለማንጸባረቅ መሥራት ይኖርባቸዋል ብለዋል። ኮሚሽኑ ያለማንም ጣልቃ ገብነት አስፈላጊውን ተግባራት በማከናወን ላይ እንደሚገኝና ምክክሩ አሁን ላይ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩንም ጠቁመዋል። ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም፤ ምክክሩ ሀገርን የምናሻግርበት፣ ለልጆቻችን ሰላም የሰፈነባትና የተረጋጋች ሀገር ለማስረከብ የምንሰራበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ነው ብለዋል። ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ይህ ምክክር የኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመው፤ የምክክሩ ስኬታማነት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዮሐንስ ሽፈራው (ዶ/ር) በመድረኩ ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ፤ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በተከተለ መልኩ መዘገብ እንደሚጠበቅባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። ለዚህም መገናኛ ብዙኃን ሊከተሏቸው የሚገቡ ዓለም አቀፍ የአዘጋገብ ስልቶችና ሙያዊ ሥነ-ምግባሮችን ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ አመልክተዋል። የመገናኛ ብዙኃን ኃላፊዎች በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱን በሰፊው በማስተዋወቅና ትክክለኛ መረጃ በማቅረብ የበኩላቸውን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወቱ ገልጸዋል።   ኮሚሽኑ በራሱ የውስጥ አቅም ያዘጋጃቸውን 15 የክልል የምክክር መድረክ ዘጋቢ ፊልሞች፣ 19 የቴሌቪዥንና የማህበራዊ ሚዲያ የቅስቀሳ መልዕክቶችን፣ 6 የሬዲዮ መልዕክቶችን እንዲሁም በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ አጫጫር መልዕክቶችን ለመገናኛ ብዙሃን አመራር አባላት አስረክቧል። ከሰኞ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መገናኛ ብዙሃን መልዕክቶቹን ወደ ሕዝብ እንደሚያደርሱ ተመልክቷል።
መከላከያ ሰራዊት በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ ነው
Jun 20, 2026 300
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦መከላከያ ሰራዊት በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) ገለጹ። የሀገር መከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ታላላቅ መርሃ ግብሮች አክብሯል።   በበዓሉ ላይ የተገኙት በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰራዊቱ የጀግንነት ታሪክ እንደ ውቅያኖስ የማይነጥፍ ከመሆኑም በላይ፣ በጭና ግንባር የተቀዳጀው ድል የጠላትን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅም ሙሉ በሙሉ የሰበረ የድል ማህተም ነው። ሰራዊቱ በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ማረጋገጫው የሰራዊቱና የህዝቡን ጠንካራ አንድነት የሚያሳየው የ"ጭና ሰማዕታት መታሰቢያ ጤና ጣቢያ" መገንባቱ እንደሆነ ጠቁመዋል። በጦር ግንባር የተሸነፈው የቀድሞው ሕወሓት እና ተላላኪዎቹ አሁንም የህዝቡን ሰላም ለማወክ በቅዥት እየተፈራገጡ መሆኑን ያነሱት አስተባባሪው፤ ጀግናው መከላከያ ሰራዊት ታሪክ መስራትና ሀገር ማዳን ልማዱ በመሆኑ የአጥፊ ቡድኖች ህልም መቼም ቢሆን እንደማይሳካ አረጋግጠዋል። የ403ኛ መከታ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል አዘዘው መኮንን በበኩላቸው፤ ኮሩ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተደቀኑ የጥፋት ፈንጂዎችን በተግባር በማምከን ከፍተኛ የሀገር ባለውለታነቱን እንዳስመሰከረ ገልጸዋል።   በሰሜኑ ህግ ማስከበር ወቅት የቀን ፀሀይ፣ የሌሊት ቁር፣ ጋራና ሸለቆ ሳይበግረው የጠላትን ሀገር የማፍረስ ህልም መና ማስቀረቱን፤ በሁሉም ግንባሮች በፈጸመው ተጋድሎ ኢትዮጵያን ከመፍረስ፣ ህዝቦቿን ደግሞ ከብተና መታደግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም መንግስትና ህዝብ የጣሉበትን አደራ በብቃት በመወጣት ጠላትን አሳፍሮ የመለሰ ታሪካዊ ኮር መሆኑን ጠቅሰዋል። ዛሬም ቢሆን ጽንፈኛውንና ተላላኪዎቹን በማንኛውም ሁኔታ መመከት የሚችል ጽኑ ሰራዊት መገንባቱን ገልጸዋል። የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዲያቆን ሸጋው ውቤ በበኩላቸው፤ የቀድሞው የህወሓት አንጃ በጭና ምድር ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው እኩይ ተግባርና የጭካኔ ድርጊት መፈጸሙን አስታውሰዋል።   ሆኖም የ403ኛ መከታ ኮር የምዕራብ ኮሪደርን በማስከፈት፣ የጥፋት ኃይሉ እኩይ ዓላማውን ለማሳካት ሲንቀሳቀስ በጭና ምድር ላይ ታሪክ ሆኖ እንዲቀር ማድረጉን ገልጸዋል። ሰራዊቱ በልማት ስራዎችም በመሳተፍ እውነተኛ የህዝብ ልጅነቱን በተግባር እያሳየ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ራሱን ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሃይል እየገነባ ነው - ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት 
Jun 20, 2026 225
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የሀገር መከላከያ ሰራዊት ራሱን ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሃይል እየገነባ መሆኑን የመከላከያ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት ገለጹ። የመከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብሯል።   የመከላከያ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት እንደገለጹት፤ ተቋም የሚገነባው በዱላ ቅብብል ነው። የመከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር እንደ ስሙ የኢትዮጵያ መከታ መሆን የጀመረው ሰራዊት የተገነባበትን አካሄድ በመውረስ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገርና ግዙፍ ሰራዊት ያላት መሆኗን በመጥቀስ፣ የተቋሙን የጀግንነት ስራዎች በተለያዩ መንገዶች መሰነድ እንደሚገባም ገልጸዋል።   የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሀይል እየተደራጀ መሆኑን ገልጸው፤ ከዘመኑ ጋር የሚራመድ ሰራዊት ተገንብቷል ብለዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙ ጥያቄና ፍላጎት አለው ያሉት ሌተናል ጀነራል መሰለ፤ ሰራዊቱ ብዙ ግዳጅ እንደሚጠብቀው በማሰብ መዘጋጀት እንዳለበት ገልጸዋል። ሰራዊቱ የሀገር ውስጥ ባንዳና ተላላኪዎችን በፍጥነት መልክ በማስያዝ ለዋናው ተቋማዊ ግዳጅ መዘጋጀት አለበት ብለዋል። ሰራዊቱ በየጊዜው በሚጎናጸፈው ድል ሳይዘናጋ ለነገ የተሻል ስራ ራሱን ማጠናከር አለበት ብለዋል።   የዕዙ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል መሰለ በለጠ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ደረጃ ለመድረስ ብዙ የህይወት መስዋዕትነት ተከፍሏል፣ ደም ፈሷል አጥንት ተከስክሷል ብለዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣትም ታሪኩን በአግባቡ መሰነድና ለትውልድ ማስተላለፍ እንዳለበት ገልጸዋል። ሰራዊት በታሪክ ይገነባል፣ በዚህም ታሪኩን ሰንዶ ለትውልድ ያስተላልፋል ብለዋል። ፈተናዎች ጀግኖችን ይወልዳሉ፣ ጀግኖችን ያፈራሉ ያሉት ሜጀር ጀነራል መሰለ በለጠ፣ የሰራዊቱ ክፍሎች የሰሩትን ታሪክ ለትውልድ በማስተላለፍ ታሪካቸውን ማስቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ከዋናው የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ርቀው የሚገኙ ዜጎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ቀጥለዋል
Jun 20, 2026 246
ሀዋሳ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ ከዋናው የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ርቀው የሚገኙ ዜጎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ፣ የፀሐይ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ። በሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ሆኮ ወረዳ የሆዲ ቦኩ ከተማ አነስተኛ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። በፕሮጀክቱ ምረቃ ወቅት የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ታዳሽ ኃይልን በመጠቀም የማህበረሰቡን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረጉት ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል።   የዚሁ አካል የሆነውና በ230 ሚሊዮን ብር የተገነባው የሆዲ ቦኩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 525 ኪሎ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን፣ ከ2 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል። የሲዳማ ክልል ውኃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር ከበደ ጋኖሌ በበኩላቸው፤ የፕሮጀክቱ ወደ ሥራ መግባት የአካባቢውን ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ብለዋል። የኃይል አቅርቦቱም የሕብረተሰቡን የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ለማሻሻል ያስችላልም ብለዋል። እንዲሁም ኢኮኖሚውን በማነቃቃት የነዋሪውን ተጠቃሚነት የሚያሳድግና ለከተማዋ ዕድገት የላቀ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ክንፈ ነጋሽ በበኩላቸው፣ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላት ለታዳሽ ኃይል ልማት ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። በተለይም ከመደበኛው የኤሌክትሪክ መስመር የራቁ አካባቢዎችን የፀሐይ ኃይል ኤሌክትሪክ ማመንጫ በመገንባት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በዚህ ሂደት በመላ አገሪቱ 43 የታዳሽ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች በመገንባት ከ10 ሺህ በላይ ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል። 525 ኪሎ ዋት የሚያመነጨው የዛሬው የሆዲ ቦኩ ፕሮጀክት የውስጥ ለውስጥ መስመር ዝርጋታና ሦስት ትራንስፎርመሮች እንዳሉትም አስረድተዋል። በፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ታድመዋል።
ሲዳማ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉ ሻምፒዮን ሆነ
Jun 20, 2026 274
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13/ 2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና ከነገሌ አርሲ ጋር አንድ አቻ በመለያየት የሊጉን ዋንጫ ማንሳቱን አረጋግጧል። ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ይሳተፋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ብርሃኑ በቀለ በመጀመሪያ አጋማሽ ማብቂያ ላይ ያስቆጠረው ጎል ሲዳማ ቡናን መሪ አድርጓል። በረከት ወልዴ በ76ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ ላይ ባሳረፈው ጎል ነገሌ አርሲ አቻ ሆኗል። የነገሌ አርሲው ቦና ቦካ በ16ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና በ65 ነጥብ ሁለት ጨዋታ እየቀረው ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ማንሳቱን አረጋግጧል። ቡድኑ በውድድር ዓመቱ ከሌሎች ተፎካካሪዎቹ በአንጻራዊነት ወጥነት ያለው አቋም ያሳየ ሲሆን ለበርካታ ሳምንታትም የሊጉ መሪ ሆኖ ቆይቷል። ሲዳማ ቡና ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎ ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣይ ዓመት በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ይሳተፋል። በሌላ በኩል ሲዳማ ቡና ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር የኢትዮጵያ ዋንጫን ለማንሳት ይፋልማል። ቡድኑ ዓመቱን በሁለት ዋንጫ የማጠናቀቅ እድል አለው። ነገሌ አርሲ በ57 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። አብዲሳ ጀማል በ19ኛው እና አብዱልሰላም ዩሱፍ በ84ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ከዘጠኝ የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ድሬዳዋ ከተማ በ38 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በሊጉም ስምንተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሸገር ከተማ በ44 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ በተደረገ የ36ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮጵያ ቡና ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። የ36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር እስከ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
የሚታይ
በስርዓት የተገነቡና ለህዝብ ቅርብ የሆኑ ተቋማትን የመፍጠር የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 20, 2026 333
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በስርዓት የተገነቡና ለህዝብ ቅርብ የሆኑ ተቋማትን የመፍጠር የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ ይህንን የገለጹት ዛሬ በተቋማት ከሚሰሩ የሪፎርም ስራዎች መካከል በደንብ ማስከበር ባለስልጣን በተቋም ግንባታ እና የሰው ሃይል ልማት በ10 ዙር ሲሰለጥኑ የነበሩ ኦፊሰሮችን ባስመረቁበት ወቅት ነው።   ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ኦፊሰሮቹ ከህዝብ ጋር አክብሮት የተሞላበት ተግባቦት እንዲኖራቸው፣ ህግና ስርዓትን ያለአንዳች አድልዎ እንዲያስከብሩ፣ ፍፁም አገልጋይነት እንዲላበሱ እና ስነምግባር የተላበሱ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። ከንቲባዋ ለደንብ ማስከበር ኦፊሰሮቹ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሲያገለግሉ ህዝባቸውን በፍቅር፣ በትህትና እንዲሁም በማክበርና ደንቦችን ያለ ምንም ርህራሄና ያለአድልዎ በማስከበር ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።   ተቋሞቻቸው በስርዓት የተገነቡ፣ ጠንካራ የአገልግሎት ስርዓት ያላቸው፣ ስነ ምግባር የተላበሱና አገልጋይ እንዲሁም ለህዝብ ቅርብ የሆኑ ባለሙያ እና አመራር የመፍጠር ተቋማዊ የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ከተማዋ የዓለም ዲፕሎማሲ ማዕከል በመሆኗ፣ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ወታደራዊ አለባበስ ዓለም አቀፍ ስታንዳርድን የጠበቀ እንዲሆን ሲጠቀሙበት ከነበረው የደንብ ልብስ ተጨማሪ ሆኖ የሚያገለግል አዲስ የደንብ ልብስ ይፋ መደረጉንም አስታውቀዋል።
ከ60 ኮርሶች 47ቱን 'A+' ያስመዘገበችው ባለብሩህ ተስፋዋ ባለዋንጫ መሃንዲስ ሩት አባተ
Jun 20, 2026 282
ዛሬ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ካስመረቃቸው 1 ሺህ 387 ተማሪዎች መካከል፣ የአንድ ሴት እጩ የመጪው ዘመን መሃንዲስ ስም በልዩ ክብርና በታላቅ ጭብጨባ አዳራሹን አናውጦታል። ይህ ስም የሩት አባተ ነው። ሩት በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ ያስመዘገበችው እጅግ አስደናቂ ውጤት የዋንጫና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ አድርጓታል። የኤሌክትሪካል ፓወር ኤንድ ኮንትሮል ኢንጅነሪንግ (Electrical Power and Control Engineering) ተማሪዋ ሩት አባተ፣ በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ ከወሰደቻቸው 60 ኮርሶች መካከል 47ቱን 'A+' እንዲሁም የቀሩትን 13 ኮርሶች 'A' በማምጣት ሙሉ 4.00 (አራት ነጥብ) ውጤት አምጥታለች። በዚህም በእጅግ ከፍተኛ ማዕረግ (Very Great Distinction) በመመረቅ የዓመቱ ኮከብ ተማሪ መሆን ችላለች።   ተወልዳ ባደገችባት አዳማ ከተማ በሚገኘው ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን በከፍተኛ ውጤት ያጠናቀቀችው ሩት፣ ለዚህ ታሪካዊ ስኬት የበቃችው ከቅድመ መደበኛ መሰረቷ ጀምሮ ባደረገችው ተከታታይ ጥረት መሆኑን ትገልጻለች። “የአዳማ ልጅ ነኝ። ከልጅነቴ ጀምሮ በቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት ነው የተማርኩት፤ ሁሌም የደረጃ ተማሪ ነበርኩ። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በትጋት እያጠናሁና እየሰራሁ ስለመጣሁ አቅሜን እያዳበርኩ እዚህ መድረስ ችያለሁ። ዩኒቨርሲቲ ስገባም ከመጀመሪያ ዓመት ጀምሮ ለትምህርቴ ልዩ ትኩረት በመስጠትና ራሴን ለፈተናዎች በአግባቡ በማዘጋጀቴ የላቀ ውጤት አምጥቻለሁ፤ ለዚህም ፈጣሪን አመሰግናለሁ” ስትል ሩት የስኬቷን ሚስጥር ታጋራለች። ይህን ታላቅ ውጤት ስታስመዘግብ ሁሌም አብረዋት የነበሩትን የቤተሰቦቿን ውለታ በኩራት ታነሳለች። ምንም ዓይነት ትኩረቷን የሚሰርቅ ነገር እንዳይገጥማት ቤተሰቦቿ ሁለንተናዊ ድጋፍ እንዳደረጉላት ትናገራለች። “ቤተሰቦቼ ሁሌም ከጎኔ ሆነው እንድበረታ አድርገውኛል። ምንም ነገር ከትምህርቴ እንዳያዘናጋኝ በመምከርና በመደገፍ አብረውኝ የስኬቴ ተጋሪ ሆነዋል። እኔም ጥረታቸውን ከንቱ አላደረግኩም፤ አላሳፈርኳቸውም" ስትል በምስጋና ትገልጻለች። ሴቶች የትኛውንም ማህበራዊና አካባቢያዊ ጫናዎች አልፈው ስኬታማ መሆን እንደሚችሉ የምትመሰክረው ሩት፣ ይህ ውጤቷ ለሌሎች እህቶቿ ትልቅ ማበረታቻና አርአያ እንደሚሆን ታምናለች።   “እኛ ሴቶች የማንበብና የመማር ዕድል ካገኘን፣ የትኛውንም ዓይነት ማኅበራዊና አካባቢያዊ ጫናዎች አልፈን ለላቀ ስኬት መብቃት እንችላለን። እኔም በቀጣይ የስኬታማ ሴቶች ህያው ምሳሌ ለመሆን ጠንክሬ እሰራለሁ።” ሩት በዚህ አሸናፊነቷ ብቻ ለመቆም አላሰበችም። በቀጣይም በትምህርቷ ላይ ይበልጥ በመበርታት የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቷን የመቀጠል እቅድ አላት። ከሁሉም በላይ ግን የተማረችውን ትምህርት ለሀገሯ በተግባር ማዋል ትልቁ ህልሟ መሆኑን ትናገራለች። "በኢነርጂውና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ለሀገሬ ጠቃሚና ችግር ፈቺ ባለሙያ ለመሆን እተጋለሁ" ስትል ጽኑ ምኞቷን ገልጻለች። ወጣቷ ባለዋንጫ መሃንዲስ ለዚህ ማዕረግ እንድትበቃ የረዷትን ፈጣሪዋን፣ ወላጆቿን፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራኖቿንና ጓደኞቿን አመስግናለች። ይህ የሩት ታሪክ የራሷ የትጋት ብቻ ሳይሆን የወላጆች የዕለት ተዕለት ክትትልና የጋራ ጥረት ውጤት ጭምር መሆኑን የእናቷ ምስክርነት ያረጋግጣል። የሩት እናት ወይዘሮ አዜብ ሻውል፣ የመጀመሪያ ልጃቸው የዋንጫ ተሸላሚ ሆና መመረቋ በቤተሰቡ ውስጥ ልዩ ደስታና ኩራት መፍጠሩን ይናገራሉ። “ሩት እድገቷ ከንባብ ተለይቶ አያውቅም፤ እጅግ ጥሩ ስነምግባር ያላት ልጅ ናት። ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ ሁሌም አንደኛ እየወጣች ነው እዚህ የደረሰችው" በማለት እናቷ የልጃቸውን የልጅነት ትጋት ያስታውሳሉ። በዩኒቨርሲቲም ቆይታዋ ሁልጊዜ ተሸላሚ መሆኗን በኩራት ያነሳሉ። እናቷ አያይዘውም፣ የሩት አባት ሁሌም የቅርብ አማካሪና አስጠኝ በመሆን ለዚህ ውጤት ትልቅ እገዛ ማድረጉን ጠቅሰው፤ “ሩት ሀገሯን የምትጠቅም ልጅ ናት፤ ወደፊትም ከዚህ በላይ ትልቅ ደረጃ እንድትደርስ እመኛለሁ” ሲሉም ገልጸዋል፡፡
መንግስት ለስፖርት ዘርፉ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል
Jun 20, 2026 350
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦መንግስት ለስፖርት ዘርፉ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት አበረታች ስኬቶች መመዝገባቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማኅበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ ገለጹ። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በስፖርት ልማት ዘርፍ ዙሪያ ከክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወይዘሮ ወርቀሰሙ ማሞ፣ የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር) ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎችና የተለያዩ የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማኅበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ በዚሁ ወቅት፤ የስፖርት ዘርፍ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ስሟ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ማድረግ አስችሏል ብለዋል፡፡ በአካልና የአእምሮ ብቁ የሆነ ትውልድን በመቅረጽና በመገንባት ረገድ የማይተካ ሚና እንዳለው ጠቁመው ይህንን ድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። ዘርፉን ዘመኑን በዋጀ አሰራርና ሕግ ለመምራት የፖሊሲና የአዋጅ ማሻሻያ ስራዎች መከናወናቸውን የጠቀሱት ሰብሳቢዋ፤ መንግስት ለስፖርቱ ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረትና በገባው ቃል መሰረት በተሰሩ የተቀናጁ ተግባራት አመርቂ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል። በተለይም ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራትና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በስፋት ተደራሽ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው፤ በስፖርት ዘርፍ ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታና በሌሎችም የስፖርት ወርቃማ ጊዜ ላይ እንገኛለን ብለዋል።   በመላ ሀገሪቱ ከ45 ሺህ በላይ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ደግሞ ከ2 ሺህ 500 በላይ የሚሆኑ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተገንብተው ለሕዝቡ ክፍት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የተገነቡት መሰረተ ልማቶች ሀገሪቱ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ውድድሮችን በብቃት እንድታስተናግድ ትልቅ አቅም መፍጠራቸውን ጠቁመዋል፡፡ በስፖርት ልማትና በስፖርት ዲፕሎማሲ ዘርፍ የተጀመሩ ስኬታማ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ርዕይ በሁሉም መስክ እየሰመረ ነው 
Jun 20, 2026 370
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ርዕይ በሁሉም መስክ እየሰመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ''ዲጂታል ለልህቀት'' በሚል መሪ ሀሳብ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ የሪፎርም ውጤቶችን የሚያሳየውን ኤግዚቢሽን መርቀው ከፍተዋል።   ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በሚቆየው ኤግዚቢሽን በጋዝና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ የፌደራል ተንቀሳቃሽ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎችን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። በተጨማሪም አሥራ ሁለት ተቋማትን ከ27 አገልግሎቶቻቸው ጋር በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን በአፍሪካ ቀዳሚ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያን በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልእክትም፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የተቋማትን አገልግሎቶች ለማዘመን ከፍተኛ ሥራዎችን መሥራቱን ጠቅሰዋል፡፡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማዘመን የተወሰዱ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎችም ለኢትዮጵያ የኩራት ምንጭ በመሆን በቴክኖሎጂ የሚመራና ዓላማ ተኮር ኢንቨስትመንት እንደሚያስገኙ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል። የሲቪል ሰርቪስ ቁልፍ የመንግሥት ተቋም ተቀይሮና ዘምኖ ማየትም ደስታን ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ወሳኝ የኢኮኖሚ መሠረተ ልማት ነው ብለዋል። ይህ ስኬት ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያ ትልሞች ምኞት ብቻ ሳይሆኑ፣ በራሳችን እጆችና አቅም የምንገነባቸው እውነታዎች መሆናቸውን በግልጽ የሚያሳይ ምስክር ነው ሲሉ አብራርተዋል። ቴክኖሎጂ የኢትዮጵያን ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና የባንክ ኢንዱስትሪ አገልግሎትና ምርታማነት በማዘመን ከፍተኛ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ስኬትም በማጠናከር፣ ልምድና ተሞክሮ ለአፍሪካውያን ወንድሞችና እህቶች በማካፈል እንዲሁም ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት ወደፊት መጓዝ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የመንግሥት ተቋማት አገልግሎቶች ማሻሻያ ከመሶብ አንድ ማዕከል ወደ ተንቀሳቃሽ በመቀጠልም ወደ ሞባይል መተግበሪያ ያደረገው ፈጣን ሽግግር በአስደናቂ ፍጥነት የታጀበ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካ ደረጃ ልክ እንደ መሶብ ሁሉም አገልግሎት በተቀናጀ ሥርዓት የሚሰጥበት የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አንድ ብላ የጀመረችው የመሶብ አገልግሎት አሁን ላይ 70 ደርሷል ብለዋል። ኢትዮጵያ ልምድ የወሰደችባቸው ሀገራት በአሥር ዓመታት ውስጥ ሰባ እንዳልደረሱ በመጠቆም፤ የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትም በአስደናቂ ፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑን ተናግረዋል። የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያው በአፍሪካ በሁሉም መስክ የመጀመሪያው የተቀናጀ የአገልግሎት መተግበሪያ ነው ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል መገልገል አስደናቂ ሆኖ ሳለ፤ ዜጎች በእጅ ስልካቸው ጉዳያቸውን ባሉበት ቦታና በየትኛውም ጊዜ መገልገል የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የመሶብ አገልግሎትም የመንግሥት አገልግሎትን ከአንድ ማዕከል ወደ ተንቀሳቃሽ፣ ከተንቀሳቃሽ ወደ የእጅ ስልክ ያሸጋገረና ጥቂት ሀገራት ብቻ የደረሱበት ስኬታማ ሥራ መሆኑን አንስተዋል። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ በብዙ ጉዳዮች ኢትዮጵያን በአፍሪካ ተምሳሌት የሚያደርጋት መሆኑን ጠቅሰው ብልፅግናን ለማረጋገጥ የበለጠ ትጋት የበለጠ ሥራ እና ልፋት እንደሚጠይቅም ጠቅሰዋል፡፡ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የኩራት ምንጭ እንዲሆኑ፣ ለልጆቿ ድህነትን የማታወርስ አገር መገንባት እንደሚገባ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ርዕይ በሁሉም መስክ እየሰመረ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጉዞ የሚሳካው በወጣት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተመራማሪዎች ቁጭት፣ ትጋትና ፈጠራ ነው
Jun 20, 2026 276
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጉዞ የሚሳካው በወጣት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተመራማሪዎች ቁጭት፣ ትጋትና ፈጠራ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎቹን የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ተመራቂዎች የሀገሪቱን የዲጂታል ሽግግርና የልማት ጉዞ መምራት እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል። የትምህርት ሥርዓቱ ከነባር ዕውቀቶች ተነሥቶ ዛሬ ላይ በኦንላይን ትምህርት እና በሰው ሠራሽ አስተውሎት የተደገፈበት ደረጃ ላይ መድረሱን ጠቅሰው፥ አሁን ያለው ትውልድም የዚህ ፈጣን የለውጥ ዘመን ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ያቀደቻቸውን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም ዕውቀት ማመንጨት፣ ቴክኖሎጂ ማልማትና ኢንዱስትሪ መገንባት የሚችሉ ሀገር ወዳድ ወጣት ባለሙያዎች ማፍራት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። መንግሥት በቀረጸው የትምህርት ፖሊሲ በመታገዝ ብቃት ያለውና ምርታማ የሰው ኃይል ለመገንባት በትጋት እየሠራ እንደሚገኝ ነው የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንደ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት ትውልድን በዕውቀት፣ በክህሎትና በሥነ ምግባር በማነጽ ረገድ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። የትናንትናዋ ኢትዮጵያ የምትችለውን ሠርታለች፤ ከዚህ በኋላ ያለችው ኢትዮጵያ ደግሞ በእናንተ ትከሻ ላይ ቆማለች ሲሉም ነው ለተመራቂዎቹ በአፅንኦት የተናገሩት። የዛሬ ተመራቂዎችም በቁጭት በመመራመርና ቴክኖሎጂ በመፍጠር ኢትዮጵያን ታላቅና የበለጸገች ሀገር ማድረግ እንደሚችሉም አስገንዝበዋል። ወጣቶች ትኩረታቸውን ከሚሰርቁ አሉታዊ አጀንዳዎች ርቀው በቁጭት በመነሣት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲፈጥሩና ሀገራቸውን እንዲቀይሩም ጥሪ አቅርበዋል። በተለይም "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ ወደ ተግባር በገባበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ የሚያስፈልጓት የሀገርና የዓለምን ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች፣ ባለ ራዕይ ተመራማሪዎችና ሥራ ፈጣሪዎች መሆናቸውን አፅንኦት ሰጥተዋል። መንግሥት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ባለሙያዎችንና ተመራቂዎችን በዘርፉ በሚፈጠሩ የሥራ ቦታዎች አወዳድሮ በማሠማራት፣ ሥራ ፈጣሪዎችንና ተመራማሪዎችን በማበረታት በፖሊሲ፣ በሕግና በአሠራር እንደሚደግፍም ገልጸዋል። እንደ ዲጂታል መታወቂያ፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ዲጂታል የፋይናንስ ሥርዓቶች እንዲሁም ሰው ሠራሽ አስተውሎት መስፋፋታቸው የመንግሥትን ዐቅምና ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በዕውቀትና በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ለማፍራትና ለነገዎቹ የኢትዮጵያ ተስፋዎች ስኬት ያልተቆጠበ ድጋፍ ለሰጡ የተመራቂ ቤተሰቦች፣ መምህራንና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ሀገር ታመሰግናችኋለች ብለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ኮሚሽኑ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስኬት ከመገናኛ ብዙኃን አመራር አባላትና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር ተወያየ
Jun 20, 2026 200
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን ለማሳካት የሚያስችል ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር መሀሙድ ድሪር፣ ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም እና ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) መገናኛ ብዙኃን እስካሁን ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነዋል። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር እንደገለጹት፤ መገናኛ ብዙኃን ለህብረተሰቡ ትክክለኛ መረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።   በተጨማሪም የሀገራዊ ምክክሩን ትክክለኛ ገጽታ ለዓለም ማኅበረሰብ ለማንጸባረቅ መሥራት ይኖርባቸዋል ብለዋል። ኮሚሽኑ ያለማንም ጣልቃ ገብነት አስፈላጊውን ተግባራት በማከናወን ላይ እንደሚገኝና ምክክሩ አሁን ላይ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩንም ጠቁመዋል። ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም፤ ምክክሩ ሀገርን የምናሻግርበት፣ ለልጆቻችን ሰላም የሰፈነባትና የተረጋጋች ሀገር ለማስረከብ የምንሰራበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ነው ብለዋል። ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ይህ ምክክር የኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመው፤ የምክክሩ ስኬታማነት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዮሐንስ ሽፈራው (ዶ/ር) በመድረኩ ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ፤ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በተከተለ መልኩ መዘገብ እንደሚጠበቅባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። ለዚህም መገናኛ ብዙኃን ሊከተሏቸው የሚገቡ ዓለም አቀፍ የአዘጋገብ ስልቶችና ሙያዊ ሥነ-ምግባሮችን ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ አመልክተዋል። የመገናኛ ብዙኃን ኃላፊዎች በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱን በሰፊው በማስተዋወቅና ትክክለኛ መረጃ በማቅረብ የበኩላቸውን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወቱ ገልጸዋል።   ኮሚሽኑ በራሱ የውስጥ አቅም ያዘጋጃቸውን 15 የክልል የምክክር መድረክ ዘጋቢ ፊልሞች፣ 19 የቴሌቪዥንና የማህበራዊ ሚዲያ የቅስቀሳ መልዕክቶችን፣ 6 የሬዲዮ መልዕክቶችን እንዲሁም በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ አጫጫር መልዕክቶችን ለመገናኛ ብዙሃን አመራር አባላት አስረክቧል። ከሰኞ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መገናኛ ብዙሃን መልዕክቶቹን ወደ ሕዝብ እንደሚያደርሱ ተመልክቷል።
መከላከያ ሰራዊት በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ ነው
Jun 20, 2026 300
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦መከላከያ ሰራዊት በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) ገለጹ። የሀገር መከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ታላላቅ መርሃ ግብሮች አክብሯል።   በበዓሉ ላይ የተገኙት በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰራዊቱ የጀግንነት ታሪክ እንደ ውቅያኖስ የማይነጥፍ ከመሆኑም በላይ፣ በጭና ግንባር የተቀዳጀው ድል የጠላትን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅም ሙሉ በሙሉ የሰበረ የድል ማህተም ነው። ሰራዊቱ በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ማረጋገጫው የሰራዊቱና የህዝቡን ጠንካራ አንድነት የሚያሳየው የ"ጭና ሰማዕታት መታሰቢያ ጤና ጣቢያ" መገንባቱ እንደሆነ ጠቁመዋል። በጦር ግንባር የተሸነፈው የቀድሞው ሕወሓት እና ተላላኪዎቹ አሁንም የህዝቡን ሰላም ለማወክ በቅዥት እየተፈራገጡ መሆኑን ያነሱት አስተባባሪው፤ ጀግናው መከላከያ ሰራዊት ታሪክ መስራትና ሀገር ማዳን ልማዱ በመሆኑ የአጥፊ ቡድኖች ህልም መቼም ቢሆን እንደማይሳካ አረጋግጠዋል። የ403ኛ መከታ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል አዘዘው መኮንን በበኩላቸው፤ ኮሩ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተደቀኑ የጥፋት ፈንጂዎችን በተግባር በማምከን ከፍተኛ የሀገር ባለውለታነቱን እንዳስመሰከረ ገልጸዋል።   በሰሜኑ ህግ ማስከበር ወቅት የቀን ፀሀይ፣ የሌሊት ቁር፣ ጋራና ሸለቆ ሳይበግረው የጠላትን ሀገር የማፍረስ ህልም መና ማስቀረቱን፤ በሁሉም ግንባሮች በፈጸመው ተጋድሎ ኢትዮጵያን ከመፍረስ፣ ህዝቦቿን ደግሞ ከብተና መታደግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም መንግስትና ህዝብ የጣሉበትን አደራ በብቃት በመወጣት ጠላትን አሳፍሮ የመለሰ ታሪካዊ ኮር መሆኑን ጠቅሰዋል። ዛሬም ቢሆን ጽንፈኛውንና ተላላኪዎቹን በማንኛውም ሁኔታ መመከት የሚችል ጽኑ ሰራዊት መገንባቱን ገልጸዋል። የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዲያቆን ሸጋው ውቤ በበኩላቸው፤ የቀድሞው የህወሓት አንጃ በጭና ምድር ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው እኩይ ተግባርና የጭካኔ ድርጊት መፈጸሙን አስታውሰዋል።   ሆኖም የ403ኛ መከታ ኮር የምዕራብ ኮሪደርን በማስከፈት፣ የጥፋት ኃይሉ እኩይ ዓላማውን ለማሳካት ሲንቀሳቀስ በጭና ምድር ላይ ታሪክ ሆኖ እንዲቀር ማድረጉን ገልጸዋል። ሰራዊቱ በልማት ስራዎችም በመሳተፍ እውነተኛ የህዝብ ልጅነቱን በተግባር እያሳየ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ራሱን ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሃይል እየገነባ ነው - ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት 
Jun 20, 2026 225
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የሀገር መከላከያ ሰራዊት ራሱን ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሃይል እየገነባ መሆኑን የመከላከያ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት ገለጹ። የመከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብሯል።   የመከላከያ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት እንደገለጹት፤ ተቋም የሚገነባው በዱላ ቅብብል ነው። የመከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር እንደ ስሙ የኢትዮጵያ መከታ መሆን የጀመረው ሰራዊት የተገነባበትን አካሄድ በመውረስ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገርና ግዙፍ ሰራዊት ያላት መሆኗን በመጥቀስ፣ የተቋሙን የጀግንነት ስራዎች በተለያዩ መንገዶች መሰነድ እንደሚገባም ገልጸዋል።   የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሀይል እየተደራጀ መሆኑን ገልጸው፤ ከዘመኑ ጋር የሚራመድ ሰራዊት ተገንብቷል ብለዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙ ጥያቄና ፍላጎት አለው ያሉት ሌተናል ጀነራል መሰለ፤ ሰራዊቱ ብዙ ግዳጅ እንደሚጠብቀው በማሰብ መዘጋጀት እንዳለበት ገልጸዋል። ሰራዊቱ የሀገር ውስጥ ባንዳና ተላላኪዎችን በፍጥነት መልክ በማስያዝ ለዋናው ተቋማዊ ግዳጅ መዘጋጀት አለበት ብለዋል። ሰራዊቱ በየጊዜው በሚጎናጸፈው ድል ሳይዘናጋ ለነገ የተሻል ስራ ራሱን ማጠናከር አለበት ብለዋል።   የዕዙ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል መሰለ በለጠ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ደረጃ ለመድረስ ብዙ የህይወት መስዋዕትነት ተከፍሏል፣ ደም ፈሷል አጥንት ተከስክሷል ብለዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣትም ታሪኩን በአግባቡ መሰነድና ለትውልድ ማስተላለፍ እንዳለበት ገልጸዋል። ሰራዊት በታሪክ ይገነባል፣ በዚህም ታሪኩን ሰንዶ ለትውልድ ያስተላልፋል ብለዋል። ፈተናዎች ጀግኖችን ይወልዳሉ፣ ጀግኖችን ያፈራሉ ያሉት ሜጀር ጀነራል መሰለ በለጠ፣ የሰራዊቱ ክፍሎች የሰሩትን ታሪክ ለትውልድ በማስተላለፍ ታሪካቸውን ማስቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በድህረ ምርጫው ወቅት ብሄራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅና የወል ትርክትን ለማጠናከር እንሰራለን
Jun 19, 2026 1894
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በድህረ ምርጫው ወቅት ብሄራዊ ጥቅምን ለማረጋገጥ፣ የህዝብን የልማት ተሳትፎ ለማሳደግ እንዲሁም የወል ትርክትን ለማጠናከር በሚያስችሉ የይዘት ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሰራተኞች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል።   የተቋሙ ሰራተኞች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ብሄራዊ ጥቅምን የሚያረጋግጡ፣ የልማት ተሳትፎን የሚያሳድጉ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጸኑ የይዘት ውጤቶች ህብረተሰቡ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው ሚና ይጫወታሉ። በአሁኑ ወቅት ያለባቸውን ድርብ ኃላፊነት በመገንዘብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ፣ የሀገርን ሰላምና ልማት የሚያጸኑ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጎለብቱ ሥራዎች ላይ ትኩረት እንደሚሰጡም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢዜአ በቅድመ ምርጫና በምርጫ ወቅት ህዝቡ ለተሳተፈበት ነፃና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እውንነት አስቻይ ምሕዳር እንዲፈጠር ከሌሎች መገናኛ ብዙሃን ጋር በመቀናጀት በርካታ ተግባራትን አከናውኗል። በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉባቸው እና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የታደሙበት የምርጫ ክርክር መድረኮች እንዲካሄዱ ማድረጉንም ገልጸዋል። የምርጫ ዘገባን በተመለከተም በጥናት ላይ የተመሠረቱ ሥራዎችን በማከናወን፤ ፍትሐዊ፣ ነጻ፣ ተዓማኒና አሳታፊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችሉ የይዘት ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቁመው፣ መገናኛ ብዙሀን ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የበኩላቸውን መወጣት የሚያስችላቸውን ስልጠናዊ ፓናል ማዘጋጀቱንም አስታውሰዋል። በድኅረ ምርጫ ወቅትም ኢዜአ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የሚያረጋግጡ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጎለብቱ፣ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግናን የሚያጠናክሩ ዘገባዎችን በስፋት እንደሚሰራም አብራርተዋል። ሐሰተኛ መረጃዎችን በማጥራት ትክክለኛ መረጃዎችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ፣ ብሎም የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ማዕከልነት ለተቀረው ዓለም ማሳየት እንደሚገባም አብራርተዋል።   የኢዜአ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ነጋሲ አምባዬ የውይይት መነሻ ሐሳብ ባቀረቡበት ወቅት፤ ለሰባተኛው ምርጫ ስኬታማነት ኢዜአን ጨምሮ መገናኛ ብዙኃን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በምርጫው ለመሳተፍ እንዲችሉና በካርዳቸው የሚፈልጉትን እንዲመርጡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይዘቶች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በድኅረ ምርጫ ወቅትም የተቋሙ ሠራተኞች አገራዊ ትብብርን የሚያጠናክሩና በጋራ መሥራትን የሚያበረታቱ ሥራዎችን መሥራት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል።   የኢዜአ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተፈራ በቀለ በበኩላቸው፤ ሕብረተሰቡን ለሰላም፣ ለልማትና ዲሞክራሲ የበለጠ የሚያሰልፉ ሥራዎችን ማከናወን ይገባል ብለዋል። በምርጫ ዋዜማ ሲወጡ የነበሩ የተሳሳቱ መረጃዎችን መመከት የሚያስችሉ ሥራዎችን መገናኛ ብዙኃን መሥራታቸውን አመልክተው፤ ኢዜአም በተናበበ አግባብ ሀሰተኛ መረጃዎችን እያጣራ እውነታውን ሲያቀርብ እንደነበር ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያደረጉት ተሳትፎ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ነው
Jun 19, 2026 1368
አዲስ አበባ፣ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያደረጉት ተሳትፎ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ኢመስበርገር ገለጹ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መካሄዱ ይታወሳል። በምርጫው ዕለት ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ከማለዳው ጀምሮ በነቂስ በመውጣት ድምጻቸውን የሰጡ ሲሆን፤ የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎችም እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ምርጫው ሲካሄድ መቆየቱ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከምርጫው ማግስት ጀምሮ የተጠናቀቁ የቆጠራ ውጤቶችን በየደረጃውና በየወቅቱ ለኅብረተሰቡ ይፋ እያደረገ ይገኛል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ኢመስበርገር፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን ተወካዮቻቸውና መሪዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ መምረጣቸውን ገልጸዋል። ይህም ሕዝቡ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት ያሳየ ጠንካራ ማረጋገጫ መሆኑን ጠቁመዋል። አምባሳደሯ አክለውም፤ ሕብረቱ ምርጫው በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ለነበራቸው ባለድርሻ አካላት መግለጫ በማውጣት ምስጋና ማቅረቡን አስታውቀዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግብዣ በተወሰኑ ጣቢያዎች ላይ ምልከታ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በዚህም ኢትዮጵያውያን ድምፃቸውን ለመስጠት በሰልፍ ቆመው ማየታቸውን እጅግ የሚያስደንቅ እንደነበር አስታውቀዋል። ይህ የምርጫ ሂደት በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ ጉዞ ውስጥ ትልቅ እና አስፈላጊ እርምጃ መሆኑንም ጠቁመዋል። በውጥረት ባለበት የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና፣ ኢትዮጵያ ምርጫ ማካሄዷ እና ሕዝቡ በሰላማዊ መንገድ ተወካዮቹን መምረጥ መቻሉ ትልቅና ጠንካራ መልዕክት እንዳለው አስገንዝበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በመደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ
Jun 19, 2026 1208
አዲስ አበባ ፣ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው 5ኛ ዓመት 12ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የከተማዋን የ2019 ዓ.ም ረቂቅ በጀትን ጨምሮ በተለያዩ ቁልፍ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚም መሰረት በመጀመሪያ በገለልተኛ የግል ተቋም የተጠናዉን የከተማዋን ገቢ የማመንጨት አቅም ጥናት ላይ ተወያይቶ ጥናቱ ይበልጥ በሁሉም ባለድርሻ አካላት በዉይይት እንዲዳብር አቅጣጫ አስቀምጧል። በሁለተኛ ደረጃ የ2019 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩ የቀጣይ ዓመት ረቂቅ በጀት 502.27 ቢሊዮን ብር ሆኖ ወደ ለከተማው ምክር ቤት እንዲመራ አቅጣጫ አስቀምጧል።   ይህ የሀብት ድልድል እና ምደባ በዋናነት የከተማ አስተዳደሩን የልማት ስትራቴጂዎች እና የትኩረት አቅጣጫዎች፣ ድህነትን ለመቀነስ፣ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማረጋገጥ፣ የነዋሪዉን የልማት ፍላጎትና የአገልግሎት አቅርቦት ለማሳደግ በተለይም የስራ እድል ፈጠራን ለሚያበረታቱ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች (መንገድ፣ ዉሃ፣ መኖሪያ ቤት፣ ፅዳት፣ ትራንስፖርትና የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል)፣ እንዲሁም ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማሻሻል ሚና ላላቸዉ ዘርፎች (ትምህርት፣ ጤና እና በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የከተማዋ ነዋሪዎች የሚደረግ ድጎማ) መስፈርቶችና ታሳቢዎች መሰረት ያደረገ ነው። በዚሁ መሰረት በከተማው አስተዳደር ለማዕከል ሴክተር ተቋማትና ለክፍለ ከተሞች ለመደበኛና ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያነት ከተደለደለው አጠቃላይ ወጪ ውስጥ፤ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው 71 በመቶ ለድህነት ቅነሳና ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የተመደበ ሲሆን፣ ቀሪው 29 በመቶ ደግሞ ለአስተዳደራዊ ወጪዎች ተደልድሏል።   በሶስተኛ ደረጃ በፍትህ ቢሮ ተዘጋጅቶ በቀረብዉ፤- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኞች የብቃት መመዘኛ እና ማረጋገጫ ተቋም ስልጠና የተግባር አደረረጃጀት እና አሰራሩን ለመወሰን በተዘጋጀዉ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በአራተኛ ደረጃ ማዘጋጃ ቤታዊ ይዞታ አገልግሎት ክፍያ ማስፈፀሚያ ረቂቅ ደንብ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በአምስተኛ ደረጃ በመሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሀገራዊ ፋይዳ ላላቸዉ ፕሮጀክቶች የቀረበ የመሬት ምደባ ላይ ተወያይቶ ካቢኔዉ ውሳኔ ማሳለፉን የከንቲባ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
በኢትዮጵያ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ብሄራዊ መግባባትን በመፍጠር አንድነትን የሚያጠናክር ነው
Jun 19, 2026 1123
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ብሄራዊ መግባባትን በመፍጠር አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም ተወካይ ሳሙኤል ዶ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የምክክር ጉባኤውን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ እንደሚያካሂድ አስታውቋል። ጉባኤውን ለማካሄድ የሚያስችል አስፈላጊ የሆኑ ዝግጅቶች እያከናወነ ይገኛል። በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም ተወካይ ሳሙኤል ዶ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ አስደናቂ ሥራ ማከናወኑን ገልጸዋል። ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የሚስተዋሉ መሠረታዊ ችግሮችን በመመካከር በመፍታት ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የምክክር ሂደት በስኬታማነት በማስቀጠል ላሳዩት ቁርጠኝነት የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ እንዲሁም ኮሚሽኑ ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል። የላይቤሪያን ተሞክሮ ጨምሮ በኮሎምቢያ፣ በላቲን አሜሪካ፣ በእስያና በተለያዩ የአፍሪካ ክፍሎች የተደረጉ ብሔራዊ ምክክሮችን ማጥናታቸውን ጠቅሰው፤ የምክክር ሂደት አማራጭ የሌለው መፍትሔ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል። ይህ ዓይነቱ ሂደት ከፍተኛ ፍላጎትን፣ ትልቅ ቁርጠኝነትን እና በጋራ ወደፊት ለመራመድ ጠንካራ ፅናትን የሚጠይቅ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሰላማዊና የምክክር አማራጮች የማኅበረሰብን የጋራ መጻኢ ዕድል ይበልጥ ብሩህ እንደሚያደርጉ አስገንዝበው፤ በርካታ ብሔረሰቦችና አስደናቂ ታሪኮች ያላትን ኢትዮጵያን ሀገራዊ አንድነትና ዘላቂ ልማት ይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ምክክር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም ኢትዮጵያውያን በምክክር ሂደቱ በንቃት በመሳተፍ ለውጤታማነቱ ገንቢ ሚና መጫወት አለባቸው ብለዋል።  
በከተማ አስተዳደሩ ህዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የሰላም አሴት ግንባታ ስራዎች መልካም ውጤት አስገኝተዋል
Jun 19, 2026 1061
ደብረ ብርሃን፤ ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፡-በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ህዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ዘላቂ ሰላምን የማጽናትና ህግ የማስከበር ተግባራት ከተማዋ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ተመራጭነቷን እንድታስቀጥል እድል መፍጠራቸውን የከተማ አስተዳደሩ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ሃላፊ አቶ ዳንኤል እሸቴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሰላምን በዘላቂነት ለማስጠበቅ ህዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የሰላም አሴት ግንባታዎች መልካም ውጤት አስገኝተዋል። በዚህም ከሀይማኖት መሪዎች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከወጣቶች፣ ከሴቶችና ከሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የተካሄዱ ህዝባዊ መድረኮች በሰላም ጉዳይ ላይ የጋራ አቋም በመውሰድ በቅንጅት ለመስራት ማስቻላቸውን ገልጸዋል። በከተማዋ ያለውን ዘላቂ ሰላም በማጽናት የኮሪደር ልማት፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችና ሌሎች የመሰረተ ግንባታዎችን በማፋጠን የከተማዋ እድገት እንዲፋጠን ማስቻሉን ጠቁመዋል። ይህም ፈጣንና ፍትሃዊ አገልግሎት በመስጠት ከተማዋ ለኢንዱስትሪ፣ ለኢንቨትስትመንት፣ ለቱሪዝምና ለንግድ የስበት ማዕከል ሆና እንድትቀጥል ማስቻሉን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በሚካሄዱ የልማት ስራዎችና በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት በመደራጀት ወጣቶችን ሴቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አስረድተዋል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ያስቻለውም ህዝቡ ለሰላምና ልማት ያለውን ጽኑ አቋም የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የተገኘውን ሰላም በዘላቂነት በማጽናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በቀጣይ አጠናክሮ በማስቀጠል የከተማውን ነዋሪ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የከተማዋ ነዋሪዎችም በሰፈርና አካባቢ አደረጃጀት በመፍጠር የአካባቢያቸውን ሰላም ነቅተው በመጠበቅ የጀመሩትን ተግባር አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ አለሜ በላይ እንደገለጹት የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ ለልማት ስራው ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር እየሰሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። የከተማ አስተዳደሩ የጀመራቸው የልማት ስራዎችም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል።
ፖለቲካ
ኮሚሽኑ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስኬት ከመገናኛ ብዙኃን አመራር አባላትና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር ተወያየ
Jun 20, 2026 200
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን ለማሳካት የሚያስችል ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር መሀሙድ ድሪር፣ ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም እና ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) መገናኛ ብዙኃን እስካሁን ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነዋል። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር እንደገለጹት፤ መገናኛ ብዙኃን ለህብረተሰቡ ትክክለኛ መረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።   በተጨማሪም የሀገራዊ ምክክሩን ትክክለኛ ገጽታ ለዓለም ማኅበረሰብ ለማንጸባረቅ መሥራት ይኖርባቸዋል ብለዋል። ኮሚሽኑ ያለማንም ጣልቃ ገብነት አስፈላጊውን ተግባራት በማከናወን ላይ እንደሚገኝና ምክክሩ አሁን ላይ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩንም ጠቁመዋል። ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም፤ ምክክሩ ሀገርን የምናሻግርበት፣ ለልጆቻችን ሰላም የሰፈነባትና የተረጋጋች ሀገር ለማስረከብ የምንሰራበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ነው ብለዋል። ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ይህ ምክክር የኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመው፤ የምክክሩ ስኬታማነት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዮሐንስ ሽፈራው (ዶ/ር) በመድረኩ ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ፤ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በተከተለ መልኩ መዘገብ እንደሚጠበቅባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። ለዚህም መገናኛ ብዙኃን ሊከተሏቸው የሚገቡ ዓለም አቀፍ የአዘጋገብ ስልቶችና ሙያዊ ሥነ-ምግባሮችን ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ አመልክተዋል። የመገናኛ ብዙኃን ኃላፊዎች በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱን በሰፊው በማስተዋወቅና ትክክለኛ መረጃ በማቅረብ የበኩላቸውን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወቱ ገልጸዋል።   ኮሚሽኑ በራሱ የውስጥ አቅም ያዘጋጃቸውን 15 የክልል የምክክር መድረክ ዘጋቢ ፊልሞች፣ 19 የቴሌቪዥንና የማህበራዊ ሚዲያ የቅስቀሳ መልዕክቶችን፣ 6 የሬዲዮ መልዕክቶችን እንዲሁም በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ አጫጫር መልዕክቶችን ለመገናኛ ብዙሃን አመራር አባላት አስረክቧል። ከሰኞ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መገናኛ ብዙሃን መልዕክቶቹን ወደ ሕዝብ እንደሚያደርሱ ተመልክቷል።
መከላከያ ሰራዊት በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ ነው
Jun 20, 2026 300
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦መከላከያ ሰራዊት በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) ገለጹ። የሀገር መከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ታላላቅ መርሃ ግብሮች አክብሯል።   በበዓሉ ላይ የተገኙት በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰራዊቱ የጀግንነት ታሪክ እንደ ውቅያኖስ የማይነጥፍ ከመሆኑም በላይ፣ በጭና ግንባር የተቀዳጀው ድል የጠላትን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅም ሙሉ በሙሉ የሰበረ የድል ማህተም ነው። ሰራዊቱ በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ የህዝባዊነትና የደግነት ምንጭ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ማረጋገጫው የሰራዊቱና የህዝቡን ጠንካራ አንድነት የሚያሳየው የ"ጭና ሰማዕታት መታሰቢያ ጤና ጣቢያ" መገንባቱ እንደሆነ ጠቁመዋል። በጦር ግንባር የተሸነፈው የቀድሞው ሕወሓት እና ተላላኪዎቹ አሁንም የህዝቡን ሰላም ለማወክ በቅዥት እየተፈራገጡ መሆኑን ያነሱት አስተባባሪው፤ ጀግናው መከላከያ ሰራዊት ታሪክ መስራትና ሀገር ማዳን ልማዱ በመሆኑ የአጥፊ ቡድኖች ህልም መቼም ቢሆን እንደማይሳካ አረጋግጠዋል። የ403ኛ መከታ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል አዘዘው መኮንን በበኩላቸው፤ ኮሩ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተደቀኑ የጥፋት ፈንጂዎችን በተግባር በማምከን ከፍተኛ የሀገር ባለውለታነቱን እንዳስመሰከረ ገልጸዋል።   በሰሜኑ ህግ ማስከበር ወቅት የቀን ፀሀይ፣ የሌሊት ቁር፣ ጋራና ሸለቆ ሳይበግረው የጠላትን ሀገር የማፍረስ ህልም መና ማስቀረቱን፤ በሁሉም ግንባሮች በፈጸመው ተጋድሎ ኢትዮጵያን ከመፍረስ፣ ህዝቦቿን ደግሞ ከብተና መታደግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም መንግስትና ህዝብ የጣሉበትን አደራ በብቃት በመወጣት ጠላትን አሳፍሮ የመለሰ ታሪካዊ ኮር መሆኑን ጠቅሰዋል። ዛሬም ቢሆን ጽንፈኛውንና ተላላኪዎቹን በማንኛውም ሁኔታ መመከት የሚችል ጽኑ ሰራዊት መገንባቱን ገልጸዋል። የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዲያቆን ሸጋው ውቤ በበኩላቸው፤ የቀድሞው የህወሓት አንጃ በጭና ምድር ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው እኩይ ተግባርና የጭካኔ ድርጊት መፈጸሙን አስታውሰዋል።   ሆኖም የ403ኛ መከታ ኮር የምዕራብ ኮሪደርን በማስከፈት፣ የጥፋት ኃይሉ እኩይ ዓላማውን ለማሳካት ሲንቀሳቀስ በጭና ምድር ላይ ታሪክ ሆኖ እንዲቀር ማድረጉን ገልጸዋል። ሰራዊቱ በልማት ስራዎችም በመሳተፍ እውነተኛ የህዝብ ልጅነቱን በተግባር እያሳየ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ራሱን ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሃይል እየገነባ ነው - ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት 
Jun 20, 2026 225
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የሀገር መከላከያ ሰራዊት ራሱን ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሃይል እየገነባ መሆኑን የመከላከያ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት ገለጹ። የመከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብሯል።   የመከላከያ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል መሰለ መሰረት እንደገለጹት፤ ተቋም የሚገነባው በዱላ ቅብብል ነው። የመከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር እንደ ስሙ የኢትዮጵያ መከታ መሆን የጀመረው ሰራዊት የተገነባበትን አካሄድ በመውረስ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገርና ግዙፍ ሰራዊት ያላት መሆኗን በመጥቀስ፣ የተቋሙን የጀግንነት ስራዎች በተለያዩ መንገዶች መሰነድ እንደሚገባም ገልጸዋል።   የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዘመኑን በዋጀ ትጥቅና የሰው ሀይል እየተደራጀ መሆኑን ገልጸው፤ ከዘመኑ ጋር የሚራመድ ሰራዊት ተገንብቷል ብለዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙ ጥያቄና ፍላጎት አለው ያሉት ሌተናል ጀነራል መሰለ፤ ሰራዊቱ ብዙ ግዳጅ እንደሚጠብቀው በማሰብ መዘጋጀት እንዳለበት ገልጸዋል። ሰራዊቱ የሀገር ውስጥ ባንዳና ተላላኪዎችን በፍጥነት መልክ በማስያዝ ለዋናው ተቋማዊ ግዳጅ መዘጋጀት አለበት ብለዋል። ሰራዊቱ በየጊዜው በሚጎናጸፈው ድል ሳይዘናጋ ለነገ የተሻል ስራ ራሱን ማጠናከር አለበት ብለዋል።   የዕዙ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል መሰለ በለጠ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ደረጃ ለመድረስ ብዙ የህይወት መስዋዕትነት ተከፍሏል፣ ደም ፈሷል አጥንት ተከስክሷል ብለዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣትም ታሪኩን በአግባቡ መሰነድና ለትውልድ ማስተላለፍ እንዳለበት ገልጸዋል። ሰራዊት በታሪክ ይገነባል፣ በዚህም ታሪኩን ሰንዶ ለትውልድ ያስተላልፋል ብለዋል። ፈተናዎች ጀግኖችን ይወልዳሉ፣ ጀግኖችን ያፈራሉ ያሉት ሜጀር ጀነራል መሰለ በለጠ፣ የሰራዊቱ ክፍሎች የሰሩትን ታሪክ ለትውልድ በማስተላለፍ ታሪካቸውን ማስቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በድህረ ምርጫው ወቅት ብሄራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅና የወል ትርክትን ለማጠናከር እንሰራለን
Jun 19, 2026 1894
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በድህረ ምርጫው ወቅት ብሄራዊ ጥቅምን ለማረጋገጥ፣ የህዝብን የልማት ተሳትፎ ለማሳደግ እንዲሁም የወል ትርክትን ለማጠናከር በሚያስችሉ የይዘት ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሰራተኞች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል።   የተቋሙ ሰራተኞች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ብሄራዊ ጥቅምን የሚያረጋግጡ፣ የልማት ተሳትፎን የሚያሳድጉ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጸኑ የይዘት ውጤቶች ህብረተሰቡ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው ሚና ይጫወታሉ። በአሁኑ ወቅት ያለባቸውን ድርብ ኃላፊነት በመገንዘብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ፣ የሀገርን ሰላምና ልማት የሚያጸኑ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጎለብቱ ሥራዎች ላይ ትኩረት እንደሚሰጡም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢዜአ በቅድመ ምርጫና በምርጫ ወቅት ህዝቡ ለተሳተፈበት ነፃና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እውንነት አስቻይ ምሕዳር እንዲፈጠር ከሌሎች መገናኛ ብዙሃን ጋር በመቀናጀት በርካታ ተግባራትን አከናውኗል። በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉባቸው እና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የታደሙበት የምርጫ ክርክር መድረኮች እንዲካሄዱ ማድረጉንም ገልጸዋል። የምርጫ ዘገባን በተመለከተም በጥናት ላይ የተመሠረቱ ሥራዎችን በማከናወን፤ ፍትሐዊ፣ ነጻ፣ ተዓማኒና አሳታፊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችሉ የይዘት ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቁመው፣ መገናኛ ብዙሀን ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የበኩላቸውን መወጣት የሚያስችላቸውን ስልጠናዊ ፓናል ማዘጋጀቱንም አስታውሰዋል። በድኅረ ምርጫ ወቅትም ኢዜአ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የሚያረጋግጡ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጎለብቱ፣ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግናን የሚያጠናክሩ ዘገባዎችን በስፋት እንደሚሰራም አብራርተዋል። ሐሰተኛ መረጃዎችን በማጥራት ትክክለኛ መረጃዎችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ፣ ብሎም የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ማዕከልነት ለተቀረው ዓለም ማሳየት እንደሚገባም አብራርተዋል።   የኢዜአ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ነጋሲ አምባዬ የውይይት መነሻ ሐሳብ ባቀረቡበት ወቅት፤ ለሰባተኛው ምርጫ ስኬታማነት ኢዜአን ጨምሮ መገናኛ ብዙኃን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በምርጫው ለመሳተፍ እንዲችሉና በካርዳቸው የሚፈልጉትን እንዲመርጡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይዘቶች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በድኅረ ምርጫ ወቅትም የተቋሙ ሠራተኞች አገራዊ ትብብርን የሚያጠናክሩና በጋራ መሥራትን የሚያበረታቱ ሥራዎችን መሥራት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል።   የኢዜአ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተፈራ በቀለ በበኩላቸው፤ ሕብረተሰቡን ለሰላም፣ ለልማትና ዲሞክራሲ የበለጠ የሚያሰልፉ ሥራዎችን ማከናወን ይገባል ብለዋል። በምርጫ ዋዜማ ሲወጡ የነበሩ የተሳሳቱ መረጃዎችን መመከት የሚያስችሉ ሥራዎችን መገናኛ ብዙኃን መሥራታቸውን አመልክተው፤ ኢዜአም በተናበበ አግባብ ሀሰተኛ መረጃዎችን እያጣራ እውነታውን ሲያቀርብ እንደነበር ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያደረጉት ተሳትፎ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ነው
Jun 19, 2026 1368
አዲስ አበባ፣ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያደረጉት ተሳትፎ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ኢመስበርገር ገለጹ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መካሄዱ ይታወሳል። በምርጫው ዕለት ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ከማለዳው ጀምሮ በነቂስ በመውጣት ድምጻቸውን የሰጡ ሲሆን፤ የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎችም እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ምርጫው ሲካሄድ መቆየቱ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከምርጫው ማግስት ጀምሮ የተጠናቀቁ የቆጠራ ውጤቶችን በየደረጃውና በየወቅቱ ለኅብረተሰቡ ይፋ እያደረገ ይገኛል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ኢመስበርገር፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን ተወካዮቻቸውና መሪዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ መምረጣቸውን ገልጸዋል። ይህም ሕዝቡ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት ያሳየ ጠንካራ ማረጋገጫ መሆኑን ጠቁመዋል። አምባሳደሯ አክለውም፤ ሕብረቱ ምርጫው በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ለነበራቸው ባለድርሻ አካላት መግለጫ በማውጣት ምስጋና ማቅረቡን አስታውቀዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግብዣ በተወሰኑ ጣቢያዎች ላይ ምልከታ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በዚህም ኢትዮጵያውያን ድምፃቸውን ለመስጠት በሰልፍ ቆመው ማየታቸውን እጅግ የሚያስደንቅ እንደነበር አስታውቀዋል። ይህ የምርጫ ሂደት በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ ጉዞ ውስጥ ትልቅ እና አስፈላጊ እርምጃ መሆኑንም ጠቁመዋል። በውጥረት ባለበት የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና፣ ኢትዮጵያ ምርጫ ማካሄዷ እና ሕዝቡ በሰላማዊ መንገድ ተወካዮቹን መምረጥ መቻሉ ትልቅና ጠንካራ መልዕክት እንዳለው አስገንዝበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በመደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ
Jun 19, 2026 1208
አዲስ አበባ ፣ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው 5ኛ ዓመት 12ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የከተማዋን የ2019 ዓ.ም ረቂቅ በጀትን ጨምሮ በተለያዩ ቁልፍ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚም መሰረት በመጀመሪያ በገለልተኛ የግል ተቋም የተጠናዉን የከተማዋን ገቢ የማመንጨት አቅም ጥናት ላይ ተወያይቶ ጥናቱ ይበልጥ በሁሉም ባለድርሻ አካላት በዉይይት እንዲዳብር አቅጣጫ አስቀምጧል። በሁለተኛ ደረጃ የ2019 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩ የቀጣይ ዓመት ረቂቅ በጀት 502.27 ቢሊዮን ብር ሆኖ ወደ ለከተማው ምክር ቤት እንዲመራ አቅጣጫ አስቀምጧል።   ይህ የሀብት ድልድል እና ምደባ በዋናነት የከተማ አስተዳደሩን የልማት ስትራቴጂዎች እና የትኩረት አቅጣጫዎች፣ ድህነትን ለመቀነስ፣ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማረጋገጥ፣ የነዋሪዉን የልማት ፍላጎትና የአገልግሎት አቅርቦት ለማሳደግ በተለይም የስራ እድል ፈጠራን ለሚያበረታቱ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች (መንገድ፣ ዉሃ፣ መኖሪያ ቤት፣ ፅዳት፣ ትራንስፖርትና የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል)፣ እንዲሁም ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማሻሻል ሚና ላላቸዉ ዘርፎች (ትምህርት፣ ጤና እና በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የከተማዋ ነዋሪዎች የሚደረግ ድጎማ) መስፈርቶችና ታሳቢዎች መሰረት ያደረገ ነው። በዚሁ መሰረት በከተማው አስተዳደር ለማዕከል ሴክተር ተቋማትና ለክፍለ ከተሞች ለመደበኛና ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያነት ከተደለደለው አጠቃላይ ወጪ ውስጥ፤ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው 71 በመቶ ለድህነት ቅነሳና ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የተመደበ ሲሆን፣ ቀሪው 29 በመቶ ደግሞ ለአስተዳደራዊ ወጪዎች ተደልድሏል።   በሶስተኛ ደረጃ በፍትህ ቢሮ ተዘጋጅቶ በቀረብዉ፤- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኞች የብቃት መመዘኛ እና ማረጋገጫ ተቋም ስልጠና የተግባር አደረረጃጀት እና አሰራሩን ለመወሰን በተዘጋጀዉ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በአራተኛ ደረጃ ማዘጋጃ ቤታዊ ይዞታ አገልግሎት ክፍያ ማስፈፀሚያ ረቂቅ ደንብ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በአምስተኛ ደረጃ በመሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሀገራዊ ፋይዳ ላላቸዉ ፕሮጀክቶች የቀረበ የመሬት ምደባ ላይ ተወያይቶ ካቢኔዉ ውሳኔ ማሳለፉን የከንቲባ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
በኢትዮጵያ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ብሄራዊ መግባባትን በመፍጠር አንድነትን የሚያጠናክር ነው
Jun 19, 2026 1123
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ብሄራዊ መግባባትን በመፍጠር አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም ተወካይ ሳሙኤል ዶ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የምክክር ጉባኤውን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ እንደሚያካሂድ አስታውቋል። ጉባኤውን ለማካሄድ የሚያስችል አስፈላጊ የሆኑ ዝግጅቶች እያከናወነ ይገኛል። በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም ተወካይ ሳሙኤል ዶ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ አስደናቂ ሥራ ማከናወኑን ገልጸዋል። ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የሚስተዋሉ መሠረታዊ ችግሮችን በመመካከር በመፍታት ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የምክክር ሂደት በስኬታማነት በማስቀጠል ላሳዩት ቁርጠኝነት የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ እንዲሁም ኮሚሽኑ ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል። የላይቤሪያን ተሞክሮ ጨምሮ በኮሎምቢያ፣ በላቲን አሜሪካ፣ በእስያና በተለያዩ የአፍሪካ ክፍሎች የተደረጉ ብሔራዊ ምክክሮችን ማጥናታቸውን ጠቅሰው፤ የምክክር ሂደት አማራጭ የሌለው መፍትሔ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል። ይህ ዓይነቱ ሂደት ከፍተኛ ፍላጎትን፣ ትልቅ ቁርጠኝነትን እና በጋራ ወደፊት ለመራመድ ጠንካራ ፅናትን የሚጠይቅ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሰላማዊና የምክክር አማራጮች የማኅበረሰብን የጋራ መጻኢ ዕድል ይበልጥ ብሩህ እንደሚያደርጉ አስገንዝበው፤ በርካታ ብሔረሰቦችና አስደናቂ ታሪኮች ያላትን ኢትዮጵያን ሀገራዊ አንድነትና ዘላቂ ልማት ይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ምክክር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም ኢትዮጵያውያን በምክክር ሂደቱ በንቃት በመሳተፍ ለውጤታማነቱ ገንቢ ሚና መጫወት አለባቸው ብለዋል።  
በከተማ አስተዳደሩ ህዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የሰላም አሴት ግንባታ ስራዎች መልካም ውጤት አስገኝተዋል
Jun 19, 2026 1061
ደብረ ብርሃን፤ ሰኔ 12/2018 (ኢዜአ)፡-በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ህዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ዘላቂ ሰላምን የማጽናትና ህግ የማስከበር ተግባራት ከተማዋ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ተመራጭነቷን እንድታስቀጥል እድል መፍጠራቸውን የከተማ አስተዳደሩ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ሃላፊ አቶ ዳንኤል እሸቴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሰላምን በዘላቂነት ለማስጠበቅ ህዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የሰላም አሴት ግንባታዎች መልካም ውጤት አስገኝተዋል። በዚህም ከሀይማኖት መሪዎች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከወጣቶች፣ ከሴቶችና ከሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የተካሄዱ ህዝባዊ መድረኮች በሰላም ጉዳይ ላይ የጋራ አቋም በመውሰድ በቅንጅት ለመስራት ማስቻላቸውን ገልጸዋል። በከተማዋ ያለውን ዘላቂ ሰላም በማጽናት የኮሪደር ልማት፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችና ሌሎች የመሰረተ ግንባታዎችን በማፋጠን የከተማዋ እድገት እንዲፋጠን ማስቻሉን ጠቁመዋል። ይህም ፈጣንና ፍትሃዊ አገልግሎት በመስጠት ከተማዋ ለኢንዱስትሪ፣ ለኢንቨትስትመንት፣ ለቱሪዝምና ለንግድ የስበት ማዕከል ሆና እንድትቀጥል ማስቻሉን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በሚካሄዱ የልማት ስራዎችና በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት በመደራጀት ወጣቶችን ሴቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አስረድተዋል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ያስቻለውም ህዝቡ ለሰላምና ልማት ያለውን ጽኑ አቋም የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የተገኘውን ሰላም በዘላቂነት በማጽናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በቀጣይ አጠናክሮ በማስቀጠል የከተማውን ነዋሪ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የከተማዋ ነዋሪዎችም በሰፈርና አካባቢ አደረጃጀት በመፍጠር የአካባቢያቸውን ሰላም ነቅተው በመጠበቅ የጀመሩትን ተግባር አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ አለሜ በላይ እንደገለጹት የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ ለልማት ስራው ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር እየሰሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። የከተማ አስተዳደሩ የጀመራቸው የልማት ስራዎችም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል።
ማህበራዊ
ከዋናው የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ርቀው የሚገኙ ዜጎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ቀጥለዋል
Jun 20, 2026 246
ሀዋሳ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ ከዋናው የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ርቀው የሚገኙ ዜጎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ፣ የፀሐይ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ። በሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ሆኮ ወረዳ የሆዲ ቦኩ ከተማ አነስተኛ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። በፕሮጀክቱ ምረቃ ወቅት የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ታዳሽ ኃይልን በመጠቀም የማህበረሰቡን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረጉት ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል።   የዚሁ አካል የሆነውና በ230 ሚሊዮን ብር የተገነባው የሆዲ ቦኩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 525 ኪሎ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን፣ ከ2 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል። የሲዳማ ክልል ውኃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር ከበደ ጋኖሌ በበኩላቸው፤ የፕሮጀክቱ ወደ ሥራ መግባት የአካባቢውን ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ብለዋል። የኃይል አቅርቦቱም የሕብረተሰቡን የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ለማሻሻል ያስችላልም ብለዋል። እንዲሁም ኢኮኖሚውን በማነቃቃት የነዋሪውን ተጠቃሚነት የሚያሳድግና ለከተማዋ ዕድገት የላቀ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ክንፈ ነጋሽ በበኩላቸው፣ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላት ለታዳሽ ኃይል ልማት ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። በተለይም ከመደበኛው የኤሌክትሪክ መስመር የራቁ አካባቢዎችን የፀሐይ ኃይል ኤሌክትሪክ ማመንጫ በመገንባት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በዚህ ሂደት በመላ አገሪቱ 43 የታዳሽ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች በመገንባት ከ10 ሺህ በላይ ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል። 525 ኪሎ ዋት የሚያመነጨው የዛሬው የሆዲ ቦኩ ፕሮጀክት የውስጥ ለውስጥ መስመር ዝርጋታና ሦስት ትራንስፎርመሮች እንዳሉትም አስረድተዋል። በፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ታድመዋል።
በስርዓት የተገነቡና ለህዝብ ቅርብ የሆኑ ተቋማትን የመፍጠር የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 20, 2026 333
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በስርዓት የተገነቡና ለህዝብ ቅርብ የሆኑ ተቋማትን የመፍጠር የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ ይህንን የገለጹት ዛሬ በተቋማት ከሚሰሩ የሪፎርም ስራዎች መካከል በደንብ ማስከበር ባለስልጣን በተቋም ግንባታ እና የሰው ሃይል ልማት በ10 ዙር ሲሰለጥኑ የነበሩ ኦፊሰሮችን ባስመረቁበት ወቅት ነው።   ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ኦፊሰሮቹ ከህዝብ ጋር አክብሮት የተሞላበት ተግባቦት እንዲኖራቸው፣ ህግና ስርዓትን ያለአንዳች አድልዎ እንዲያስከብሩ፣ ፍፁም አገልጋይነት እንዲላበሱ እና ስነምግባር የተላበሱ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። ከንቲባዋ ለደንብ ማስከበር ኦፊሰሮቹ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሲያገለግሉ ህዝባቸውን በፍቅር፣ በትህትና እንዲሁም በማክበርና ደንቦችን ያለ ምንም ርህራሄና ያለአድልዎ በማስከበር ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።   ተቋሞቻቸው በስርዓት የተገነቡ፣ ጠንካራ የአገልግሎት ስርዓት ያላቸው፣ ስነ ምግባር የተላበሱና አገልጋይ እንዲሁም ለህዝብ ቅርብ የሆኑ ባለሙያ እና አመራር የመፍጠር ተቋማዊ የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ከተማዋ የዓለም ዲፕሎማሲ ማዕከል በመሆኗ፣ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ወታደራዊ አለባበስ ዓለም አቀፍ ስታንዳርድን የጠበቀ እንዲሆን ሲጠቀሙበት ከነበረው የደንብ ልብስ ተጨማሪ ሆኖ የሚያገለግል አዲስ የደንብ ልብስ ይፋ መደረጉንም አስታውቀዋል።
የመደመር መንግሥት የሲቪል ሰርቪስ ውጤታማ ሪፎርም የአገልግሎት ጥራት በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
Jun 20, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት የሲቪል ሰርቪስ ውጤታማ ሪፎርም የአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፋናን በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ''ዲጂታል ለልህቀት'' በሚል መሪ ሀሳብ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ የሪፎርም ውጤቶችን የሚያሳየውን ኤግዚቢሽንና ጉባኤን መርቀዋል። ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በሚቆየው ኤግዚቢሽን በጋዝና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ የፌደራል ተንቀሳቃሽ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎችን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። በተጨማሪም አሥራ ሁለት ተቋማትን ከ27 አገልግሎቶቻቸው ጋር በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን በአፍሪካ ቀዳሚ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያን በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። በመድረኩ ላይ የሁለቱ ምክር ቤተች አፈ ጉባኤዎች፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች፣ ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል መንግሥታት የሥራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። በዚሁ ወቅት የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ዘመናዊ የመንግሥትና የአገልግሎት አስተዳደር ዘመናትን ቢቆጠርም ዕድገት ከማፋጠን አኳያ ክፍተቶች ነበሩበት ብለዋል። ሀገራዊ ለውጡ የወለደው የመደመር መንግሥትም የሲቪል ሰርቪስ የአገልግሎት ለውጥን በማያመጣና ዕድገትን በማያፋጥን ማነቆ የተተበተበ መሆኑን በግልፅ መገንዘቡን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተደረሰው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ በገፅ 129 ላይ ከለውጡ በፊት የተደረጉ ሪፎርሞች የሀገራዊ ልማት ላይ ያለመመስረት እና በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ሳቢያ ለድክመት የተጋለጡ መሆናቸውን በግልፅ መመላከቱን አስረድተዋል። በዚህም የመደመር መንግሥት የተቋማትን ልዩ ባህሪና የሴክተሮችን ፍላጎት ታሳቢ በማድግ ጠንካራ ሥርዓት መገንባት የሚያስችል ሀገር በቀል የሪፎርም እርምጃ መወሰዱን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያን የሲቪል ሰርቪስ የአገልግሎት ምኅዳር ለማዘመን የተከናወኑ የሪፎርም እርምጃዎችም በዝግጅ፣ በትግበራና በማፅናት ምዕራፍ የሚያልፉበትን ውጤታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የተገልጋዮችን ቅሬታ መፍትሔ በመስጠት ቀልጣፋ የአገልግሎት አቅም እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ ተምሳሌታዊ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም በአፍሪካና ዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ዕውቅና እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል። ተቀማትም በመደመር መንግሥት መርህ የዜጎችን የአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፋና የሚያዘምን ምኅዳር በመገንባት የተገኘውን ስኬት ማጎልበት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም ለማህበረሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማሰናሰል የአገልግሎት ደረጃን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። በቀጣይም ሲቪል ሰርቪሱን የበለጠ ለማዘመን የአመራሩን ቁርጠኝነትና የትውልድን ትጋት የሚሻ ወሳኝ ሀገራዊ የልማት አጀንዳ መሆኑንም አስገንዝበዋል።  
የክልሉ መንግስት ስደተኞችን ተጠቃሚ ያደረገ የልማት ስራዎች እያከናወነ ነው
Jun 20, 2026 208
አሶሳ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የክልሉ መንግስት ስደተኞችን ተጠቃሚ ያደረገ የልማት ስራዎች እያከናወነ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን ተናገሩ። ዓለም አቀፍ የስደተኞች ቀን በክልሉ ኡራ ወረዳ የስደተኞች ጣቢያ ተከብሯል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ክልሉ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞችን ከመቀበል ባለፈ ስደተኞችን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።   በክልሉ አራት መጠለያ ጣቢያዎች ላይ ከ112 ሺህ በላይ ስደተኞች እንደሚገኙ ገልፀው ፥ ስደተኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ጠንካራ መስተጋብር በመፍጠር በአብሮነት እየኖሩ ነው ብለዋል። ‎ስደተኞች የውሃ፣ የትምህርት የጤናና ሌሎች የመሠረተ ልማቶችን ከተቀባዩ ማህበረሰብ እኩል ተጠቃሚ መሆናቸው የኢትዮጵያን ስደተኞች አያያዝ የተሻለ ተሞክሮ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ጠይባ ሀሰን በበኩላቸው፣ በኢትዮጵያ በስደተኞች አያያዝ አመቺ መሆኗ በትልልቅ ዓለምአቀፍ ተቋማት ጭምር ዕውቅና ማግኘቷን ጠቅሰዋል። ‎ ‎ዓለም አቀፍ የስደተኞች ቀን ሲከበርም በመላው ዓለም በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ስደተኞችን እውቅና ለመስጠት እና ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለማጠናከር ያለመ እንደሆነ አስታውቀዋል። ‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስትና ሕዝብ ለስደተኞች የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመክፈት ያሳየው ምላሽ የሚደነቅ መሆኑንም አንስተዋል።   በክልሉ በሚገኙ ስደተኞች የክልሉ መንግስት እና ማህበረሰብ እያደረጉት ያለው ሰብአዊ ድጋፍ እና የሚስተዋለው ማህበራዊ መስተጋብር የሚደነቅ ነው ያሉት ደግሞ በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ባርሃም ሳሊ ናቸው።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃትና ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ ሚና እያበረከተ ነው 
Jun 20, 2026 484
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃትና ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በብዝኃ ኢኮኖሚ መርህ ላይ በመመስረት በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እንዲሁም በኢንዱስትሪ ዘርፎች ሰፊ እምርታዊ ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች። ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪው ረገድ ወደ ላቀ ምዕራፍ ላይ እንድትደርስና በዘርፉ የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ ታስቦ የተወጠነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ዘንድሮ ለአራተኛ ጊዜ በስኬት ተካሂዷል። በዚህም የኢትዮጵያን ተወዳዳሪነት የሚያሳዩ አዳዲስ የኢንዱስትሪ ቴክኖሎጂዎችና ሌሎችም ቀርበው በስኬታማነት ተከናውኗል፡፡ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን በማነቃቃት ረገድ ባለፉት ዓመታት ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ ስኬቶችን አስመዝግቧል፡፡ ንቅናቄው የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን በማሳደግና መዋቅራዊ ሽግግርን በማምጣት ለሀገሪቱ ኢንዱስትሪዎች ጠንካራ መሠረት መጣሉንም ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ለውጥ መጥቷል፤ የገቢ ንግድን በአገር ውስጥ ምርቶች በመተካት የውጭ ምንዛሬን ማዳን መቻሉን እንዲሁም የባለሀብቱን ተሳትፎና የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንትን በማሳደግ ረገድ ትልልቅ ስኬቶች ማስመዝገቡን ተናግረዋል፡፡ መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት መዋቅራዊ ሽግግሩ በፈጣን ሁኔታ ለውጥ በማሳየት ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡ ግንዛቤን በማስጨበጥ፣ ቀጣይነት ያለውና ጥራት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመጣ በማድረግ እንዲሁም የኢንዱስትሪዎች ተወዳዳሪነት ጎልቶ እንዲታይ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል። የአምራች ኢንዱስትሪው የማምረት አቅምና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ጠቅሰው የኢንዱስትሪው አጠቃላይ የማምረት አቅም አጠቃቀም 66 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል። የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በተደረጉት መዋቅራዊ ለውጦች ምክንያት በሁሉም ዘርፍ የተሻሉ ውጤቶች እየታዩ መሆናቸውን ጠቅሰው ዘርፉ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ይዞ ከመምጣቱም በላይ ለሀገራዊ ብልጽግና መረጋገጥ ትልቅ አቅም እየሆነ ይገኛል ብለዋል፡፡
በወላይታ ዞን በዘንድሮ መኸር እርሻ ከ132 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል
Jun 20, 2026 258
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በዘንድሮው የመኸር ወቅት ከ132 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዘማች ሶርሳ (ዶ/ር)ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው መኸር እርሻ 132 ሺህ 776 ሄክታር መሬት በአዝዕርትና በሆርቲካልቸር ሰብሎች ይለማል። ከሚለማው መሬትም ከ19 ሚሊዮን 96 ሺህ 767 ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ግብ ተቀምጦ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የመኸር ወቅት የግብርና ልማቱን ውጤታማ ለማድረግና ምርታማነትን ለማሳደግም 112 ሺህ 979 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑን ኃላፊው ገልጸዋል። በዞኑ ከሚለማው መሬት አብዛኛው በሜካናይዜሽን የሚታረስና በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑንም ጠቁመዋል። አርሶ አደሮች በጋራ አልምተው ውጤታማ እንዲሆኑ መምሪያው ከግብዓት አቅርቦት ጀምሮ የባለሙያ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም አስረድተዋል።   ኢዜአ ያነጋገራቸው የዳሞት ዋጃ ቀበሌ አርሶ አደሮች ፤ በመኸር እርሻ የተሻለ ውጤት ለማግኘት ማሳቸውን እያዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል። የግብርና ባለሙያዎችም የሙያ ምክር ከመስጠት ጀምሮ በተለያየ መንገድ እያገዟቸው መሆኑን ተናግረዋል።   የዋጃ ቀሮ ቀበሌ አርሶ አደር ወይዘሮ ቆንጂት ዋትሮ በበኩላቸው፤ ማሳቸውን በተደጋጋሚ በማረስ ለዘር ዝግጁ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ አመራሩ ነባራዊ ሁኔታን በአግባቡ በመረዳት ጥረቱን ማጠናከር አለበት
Jun 20, 2026 293
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦የተለመደውን አሠራር በመከተል የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነትን ማረጋገጥ ስለማይቻል አመራሩ ነባራዊ ሁኔታውን በአግባቡ በመረዳት ጥረቱን ማጠናከር አለበት ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራው ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል አመራሮች ቡድን የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ጎብኝቷል። በዚሁ ጊዜ ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት የተለመደውን አሠራር በመከተል የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነትን ማረጋገጥ ስለማይቻል የለውጥ አመራሩ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ አስቀድሞ በመረዳት ስትራቴጂዎች ቀርጾ መንቀሳቀስ አለበት።   የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞንም በዚህ መነሻነት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ውስጥ መግባቱን ገልጸዋል። ገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ዓላማን በማሳካት ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑንም ጠቁመዋል። ልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ የመሠረተ ልማት ዝግጅት ምዕራፍን በማለፍ ካፒታል፣ ምርታማነትና ከተሜነት የሚገናኙበትና የጋራ ፍሰታቸውን የሚያጠናክሩበት መሆኑንም ተናግረዋል። እስካሁን ባለው እንቅስቃሴ የንግድና ሎጂስቲክስ፣ ግብርና ምርት ማቀነባበር፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን፣ አገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች በዞኑ ወደ ሥራ ገብተዋልም ነው ያሉት። በእነዚህ ሥራዎች ላይ ኢትዮጵያውያን ባለሀብቶችን ጨምሮ የቻይና፣ የአሜሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የሆላንድ፣ የጣሊያንና የሌሎች አገራት ኢንቨስተሮች እንደሚገኙም አንስተዋል።   የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን የሚያረጋግጡ እነዚህን ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች በማጠናከር፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነትን ይበልጥ የሚያሳድግ ይሆናል ብለዋል። በዚህ ጉብኝት ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማክሮ ኢኮኖሚ አማካሪ አምባሳደር ግርማ ብሩ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልልና የፌዴራል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በክልሉ ከተሞችን ዘመናዊና ምቹ የመኖሪያ አካባቢ የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል
Jun 20, 2026 240
ቡታጅራ ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተሞችን ዘመናዊና ምቹ የመኖሪያ አካባቢ የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለጸ። የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጨምር ኃይሌ፤ በክልሉ በተለያዩ ከተሞች ሁሉን አቀፍ የሆነ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። የከተሞቹ ልማት የአስፋልት መንገዶችን ጨምሮ፣ የእግረኞች እና የሳይክል መንገድ እንዲሁም ለመዝናኛ ምቹ የሆኑ አረንጓዴ ስፍራዎችን በማካተት ግንባታው እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በዚህ ረገድ ቡታጅራ ከተማ በኮሪደር ልማትም ይሁን በወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክት የምትጠቀስ መሆኗን አንስተው፣ በሌሎች የክልሉ ማዕከል ከተሞችም መቀጠሉን ተናግረዋል። የወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክት ከቡታጅራ በተጨማሪ በወራቤ ከተማም እየተሠራ መሆኑን አንስተው፣ በክልሉ ከተሞችን ዘመናዊና ምቹ የመኖሪያ አካባቢ የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በሰባት የክልል ማዕከል ከተሞች 165 ኪሎ ሜትር ኮሪደር ልማት በሁለት ምዕራፍ ግንባታቸውን ለማጠናቀቅ በተቀናጀ መልኩ እየተሠራ መሆኑን አንስተው፣ አሁን ላይ 61 ኪሎ ሜትር ተጠናቆ ለአገልግሎት በቅቷል ብለዋል። በክልሉ የገጠር ኮሪደር ልማትን በልዩ ትኩረት በመሥራት የአርሶ አደሮችን አኗኗር ከማሻሻል ባለፈ ከከተሞች ጋር የማስተሳሰር ሥራ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢንስቲትዩቱ የፍትህ ዘርፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 20, 2026 240
አዳማ፣ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ሕግ ምርምርና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የፍትህ ዘርፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ። ኢንስቲትዩቱ የፍትህ ሪፎርሙን ለማሳካት ያካሄዳቸውን የምርምር ውጤቶች በግብዓት ለማዳበር የሚያስችል የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አባገዳ አዳራሽ በማካሄድ ላይ ይገኛል።   የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት አቶ ገዛሊ አባ ሲመል ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት በጥናትና ምርምር የተደገፉ የመፍትሔ ሐሳቦችን እያቀረበ ይገኛል። በመድረኩ ላይ በቁልፍ የፍትህ ዘርፍ ጉዳዮች ዙሪያ የተከናወኑ አምስት የተለያዩ የምርምር ውጤቶች እንደሚቀርቡ ተናግረዋል። ምርምሮቹም የፍትህ አካላት ስነ-ምግባር፣ የፌዴራልና የክልል የህግ ተፈፃሚነት ወሰን ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶች፣ በፍትህ ዘርፉ የዲጂታል አገልግሎት ዘመን የቋሚና ተዘዋዋሪ ችሎት አስፈላጊነት፣ እንዲሁም የህግ ትርጓሜና የተፈፃሚነት ወሰን የተመለከቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህ የምርምር ውጤቶች ጠንካራ የፍትህ ስርዓት በመገንባት በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የፍትህ ዘርፍ ሪፎርም ለማሳካት ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተለይም በህግና በአሰራር ዙሪያ ያሉትን ክፍተቶች ለመድፈን በእጅጉ ያግዛሉ ብለዋል። የኦሮሚያ ህግ ምርምርና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ አዱኛ ሙሐመድ በበኩላቸው፤ ኢንስቲትዩቱ በክልሉ የፍትህ ስርዓትን ለማሻሻል እስካሁን ከ100 በላይ የምርምር ስራዎችን በማካሄድ በግብዓትነት እንዲያገለግሉ ማድረጉን ጠቁመዋል።   በተለይም በዘርፉ የተጀመሩ የሪፎርምና የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ስራዎችን ለማሳለጥ በጥናትና ምርምር ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ የፍትህ ስርዓቱን አሰራር ለማዘመንና በቴክኖሎጂ ለመምራት የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ለዛሬው መድረክ መቅረባቸውን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ ከጥናትና ምርምር ስራዎች ጎን ለጎን፣ ብቁ የፍትህ አካላትን ለማፍራትና ጥራትን ለማረጋገጥ ለህግ ባለሙያዎች የስልጠናና የአቅም ግንባታ ስራዎችን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝም ዋና ዳይሬክተሯ አክለዋል።   በመድረኩ ላይ በፌዴራልና በክልል የሕግ ወሰን ተፈጻሚነት ዙሪያ የተካሄደውን ምርምር ያቀረቡት አብዲሳ ጉርሜ (ዶ/ር)፤ የጥናቱ ውጤት በፌዴራልና በክልል የሕግ ተፈጻሚነት ረገድ የሚታዩ ውስንነቶችን በግልጽ በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከቱን አስገንዝበዋል። በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ከኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እና ከፌዴራል ፍትህ ኢንስቲትዩት የተጋበዙ ተመራማሪዎችና የህግ ምሁራን በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዘመናዊ የአገልግሎት ምኅዳር የመንግሥትና ሕዝብን አመኔታ የሚያጎለብት አቅም እየገነባ ነው
Jun 20, 2026 153
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዘመናዊ የአገልግሎት ምኅዳር የመንግሥትና ሕዝብን አመኔታ የሚያጎለብት አቅም እየገነባ መሆኑን የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ''ዲጂታል ለልህቀት'' በሚል መሪ ሐሳብ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን፣ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ የሪፎርም ውጤቶችን የሚያሳየውን ኤግዚቢሽንና ጉባኤ መርቀዋል። ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በሚቆየው ኤግዚቢሽን፤ በጋዝና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ የፌደራል ተንቀሳቃሽ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎችን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። በተጨማሪም አሥራ ሁለት ተቋማትን ከ27 አገልግሎቶቻቸው ጋር በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን፣ በአፍሪካ ቀዳሚ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያን በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) በፓናል ውይይት ላይ እንደገለጹት፤ የመንግሥት አገልግሎትን ለማዘመን የአፍሪካና ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚና አስተዳደር አብዮት ተሞክሮዎችን መቀመር ተችሏል። ይህም የኢትዮጵያን የመንግሥት አገልግሎቶች ተግዳሮቶች ለመቅረፍ ዘመናዊ የፖሊሲና ፕሮግራም፣ አዋጅና ደንብ፣ መመሪያና ስታንዳርድ መቅረፅ የሚያስችል ሪፎርም ማካሄድ እንዳስቻለ ገልጸዋል። በዚህም የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ የፈጠረው ምኅዳር ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ከብቁ የሰው ኃይል በማሰናሰል ፍሬያማ ውጤት እያስገኘ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ቴክኖሎጂን ከብቁ የሰው ኃይል ያቀናጀ ቁርጠኛ አገልግሎት ይፈልጋል ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንግሥት አገልግሎትም ከቴክኖሎጂ ጋር የተጣጣመ ዘመናዊ የአገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር የመንግሥትና ሕዝብን አመኔታ እያጎለበተ መሆኑን ገልጸዋል። የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድግ ምኅዳር ማጠናከር ያስፈልጋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የመሶብ አንድ ማዕከል የዲጂታል አገልግሎትም የተገልጋዮችን እንግልት በመቀነስ ረገድ ጉልህ ፋይዳ እያስገኘ ነው ብለዋል።   የፌደራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ ዓለማየው፤ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት የተገልጋዮችን እንግልት በመቅረፍ የአገልግሎት እርካታን እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። በአንድ ዓመት ውስጥ ተግባራዊ በተደረገው ውጤታማ የሪፎርም እርምጃም ከፌደራል እስከ ክልል ድረስ 70 የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎቶችን ወደ ሥራ ማስገባት እንደተቻለ ገልጸዋል። መሶብ ወደ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ተሸጋግሯል ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ በቀጣይም ሁሉንም የመንግሥት አገልግሎቶች በመሶብ የአንድ ማዕከል ለማካተት በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል። በፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የተቋማት ሪፎርም ዋና ዳይሬክተር አሰፋ በየነ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ሪፎርም አገልግሎትን በማዘመን የአገልግሎት ጥራትን የሚያሳደግ ምኅዳር እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የሪፎርሙን ዘላቂነትና ውጤታማነት ለማሳደግ የአመራር ቁርጠኝነትና የቴክኖሎጂ ትግበራ ቀጣይነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የተቋማት አቅም ግንባታን በማጠናከር፣ የሰው ኃይልና ትውልድን ከቴክኖሎጂ ጋር የማብቃት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መክረዋል።  
ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ርዕይ በሁሉም መስክ እየሰመረ ነው 
Jun 20, 2026 370
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ርዕይ በሁሉም መስክ እየሰመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ''ዲጂታል ለልህቀት'' በሚል መሪ ሀሳብ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ የሪፎርም ውጤቶችን የሚያሳየውን ኤግዚቢሽን መርቀው ከፍተዋል።   ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በሚቆየው ኤግዚቢሽን በጋዝና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ የፌደራል ተንቀሳቃሽ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎችን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። በተጨማሪም አሥራ ሁለት ተቋማትን ከ27 አገልግሎቶቻቸው ጋር በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን በአፍሪካ ቀዳሚ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያን በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልእክትም፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የተቋማትን አገልግሎቶች ለማዘመን ከፍተኛ ሥራዎችን መሥራቱን ጠቅሰዋል፡፡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማዘመን የተወሰዱ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎችም ለኢትዮጵያ የኩራት ምንጭ በመሆን በቴክኖሎጂ የሚመራና ዓላማ ተኮር ኢንቨስትመንት እንደሚያስገኙ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል። የሲቪል ሰርቪስ ቁልፍ የመንግሥት ተቋም ተቀይሮና ዘምኖ ማየትም ደስታን ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ወሳኝ የኢኮኖሚ መሠረተ ልማት ነው ብለዋል። ይህ ስኬት ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያ ትልሞች ምኞት ብቻ ሳይሆኑ፣ በራሳችን እጆችና አቅም የምንገነባቸው እውነታዎች መሆናቸውን በግልጽ የሚያሳይ ምስክር ነው ሲሉ አብራርተዋል። ቴክኖሎጂ የኢትዮጵያን ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና የባንክ ኢንዱስትሪ አገልግሎትና ምርታማነት በማዘመን ከፍተኛ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ስኬትም በማጠናከር፣ ልምድና ተሞክሮ ለአፍሪካውያን ወንድሞችና እህቶች በማካፈል እንዲሁም ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት ወደፊት መጓዝ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የመንግሥት ተቋማት አገልግሎቶች ማሻሻያ ከመሶብ አንድ ማዕከል ወደ ተንቀሳቃሽ በመቀጠልም ወደ ሞባይል መተግበሪያ ያደረገው ፈጣን ሽግግር በአስደናቂ ፍጥነት የታጀበ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካ ደረጃ ልክ እንደ መሶብ ሁሉም አገልግሎት በተቀናጀ ሥርዓት የሚሰጥበት የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አንድ ብላ የጀመረችው የመሶብ አገልግሎት አሁን ላይ 70 ደርሷል ብለዋል። ኢትዮጵያ ልምድ የወሰደችባቸው ሀገራት በአሥር ዓመታት ውስጥ ሰባ እንዳልደረሱ በመጠቆም፤ የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትም በአስደናቂ ፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑን ተናግረዋል። የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያው በአፍሪካ በሁሉም መስክ የመጀመሪያው የተቀናጀ የአገልግሎት መተግበሪያ ነው ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል መገልገል አስደናቂ ሆኖ ሳለ፤ ዜጎች በእጅ ስልካቸው ጉዳያቸውን ባሉበት ቦታና በየትኛውም ጊዜ መገልገል የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የመሶብ አገልግሎትም የመንግሥት አገልግሎትን ከአንድ ማዕከል ወደ ተንቀሳቃሽ፣ ከተንቀሳቃሽ ወደ የእጅ ስልክ ያሸጋገረና ጥቂት ሀገራት ብቻ የደረሱበት ስኬታማ ሥራ መሆኑን አንስተዋል። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ በብዙ ጉዳዮች ኢትዮጵያን በአፍሪካ ተምሳሌት የሚያደርጋት መሆኑን ጠቅሰው ብልፅግናን ለማረጋገጥ የበለጠ ትጋት የበለጠ ሥራ እና ልፋት እንደሚጠይቅም ጠቅሰዋል፡፡ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የኩራት ምንጭ እንዲሆኑ፣ ለልጆቿ ድህነትን የማታወርስ አገር መገንባት እንደሚገባ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ርዕይ በሁሉም መስክ እየሰመረ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነውን የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያን መረቁ
Jun 20, 2026 304
‎አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) '‘ዲጂታል ለልህቀት'’ በሚል ስያሜ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ፣ በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን፣ በአፍሪካ ቀዳሚ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ዛሬ በይፋ መርቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‎ይህ ታላቅ ስኬት ለሀገራችን ከፍተኛ ኩራት ከመሆኑም በላይ በቴክኖሎጂ የሚመራ እና ዓላማ ተኮር ኢንቨስትመንት ምን ሊያስገኝ እንደሚችል ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል።   የኢኮኖሚ ወሳኝ መሠረተ ልማት የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የዜጎችን ጊዜ ይቆጥባል፣ የሙስና ቀዳዳዎችን ይደፍናል፣ እንዲሁም በመንግሥት በኩል የተቋማትን ታማኝነትና ጥንካሬ ያጎለብታል ሲሉም ገልጸዋል። ‎‎ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያ ትልሞች ተራ ምኞት ሳይሆኑ፣ በራሳችን እጆችና አቅም የምንገነባቸው እውነታዎች መሆናቸውን በግልጽ የሚያሳይ ምስክር ነውም ብለዋል።   ይህን ስኬት እንድናጠናክር፣ ተሞክሯችንን ለአፍሪካውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እንድናካፍል፣ እንዲሁም ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት እንድንጓዝ በማለት ጥሪ አቅርበዋል ፡፡
ስፖርት
ሲዳማ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉ ሻምፒዮን ሆነ
Jun 20, 2026 274
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13/ 2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና ከነገሌ አርሲ ጋር አንድ አቻ በመለያየት የሊጉን ዋንጫ ማንሳቱን አረጋግጧል። ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ይሳተፋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ብርሃኑ በቀለ በመጀመሪያ አጋማሽ ማብቂያ ላይ ያስቆጠረው ጎል ሲዳማ ቡናን መሪ አድርጓል። በረከት ወልዴ በ76ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ ላይ ባሳረፈው ጎል ነገሌ አርሲ አቻ ሆኗል። የነገሌ አርሲው ቦና ቦካ በ16ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና በ65 ነጥብ ሁለት ጨዋታ እየቀረው ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ማንሳቱን አረጋግጧል። ቡድኑ በውድድር ዓመቱ ከሌሎች ተፎካካሪዎቹ በአንጻራዊነት ወጥነት ያለው አቋም ያሳየ ሲሆን ለበርካታ ሳምንታትም የሊጉ መሪ ሆኖ ቆይቷል። ሲዳማ ቡና ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎ ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣይ ዓመት በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ይሳተፋል። በሌላ በኩል ሲዳማ ቡና ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር የኢትዮጵያ ዋንጫን ለማንሳት ይፋልማል። ቡድኑ ዓመቱን በሁለት ዋንጫ የማጠናቀቅ እድል አለው። ነገሌ አርሲ በ57 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። አብዲሳ ጀማል በ19ኛው እና አብዱልሰላም ዩሱፍ በ84ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ከዘጠኝ የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ድሬዳዋ ከተማ በ38 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በሊጉም ስምንተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሸገር ከተማ በ44 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ በተደረገ የ36ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮጵያ ቡና ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። የ36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር እስከ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
መንግስት ለስፖርት ዘርፉ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል
Jun 20, 2026 350
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦መንግስት ለስፖርት ዘርፉ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት አበረታች ስኬቶች መመዝገባቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማኅበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ ገለጹ። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በስፖርት ልማት ዘርፍ ዙሪያ ከክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወይዘሮ ወርቀሰሙ ማሞ፣ የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር) ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎችና የተለያዩ የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማኅበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ በዚሁ ወቅት፤ የስፖርት ዘርፍ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ስሟ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ማድረግ አስችሏል ብለዋል፡፡ በአካልና የአእምሮ ብቁ የሆነ ትውልድን በመቅረጽና በመገንባት ረገድ የማይተካ ሚና እንዳለው ጠቁመው ይህንን ድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። ዘርፉን ዘመኑን በዋጀ አሰራርና ሕግ ለመምራት የፖሊሲና የአዋጅ ማሻሻያ ስራዎች መከናወናቸውን የጠቀሱት ሰብሳቢዋ፤ መንግስት ለስፖርቱ ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረትና በገባው ቃል መሰረት በተሰሩ የተቀናጁ ተግባራት አመርቂ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል። በተለይም ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራትና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በስፋት ተደራሽ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው፤ በስፖርት ዘርፍ ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታና በሌሎችም የስፖርት ወርቃማ ጊዜ ላይ እንገኛለን ብለዋል።   በመላ ሀገሪቱ ከ45 ሺህ በላይ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ደግሞ ከ2 ሺህ 500 በላይ የሚሆኑ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተገንብተው ለሕዝቡ ክፍት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የተገነቡት መሰረተ ልማቶች ሀገሪቱ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ውድድሮችን በብቃት እንድታስተናግድ ትልቅ አቅም መፍጠራቸውን ጠቁመዋል፡፡ በስፖርት ልማትና በስፖርት ዲፕሎማሲ ዘርፍ የተጀመሩ ስኬታማ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
በዓለም ዋንጫው ኮትዲቯር ከጀርመን የሚያደርጉት ጨዋታ ትኩረትን ስቧል
Jun 20, 2026 292
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ አምስት መርሐ ግብር ኮትዲቯር ከጀርመን ጋር ዛሬ ጨዋታዋን ታከናውናለች። ጨዋታው ከምሽቱ አምስት ሰዓት ላይ በቶሮንቶ ስታዲየም ይከናወናል። የምዕራብ አፍሪካዋ ኮትዲቯር በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ ኢኳዶርን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ይህም በዘንድሮው ዓለም ዋንጫ ድል የቀናት የመጀመሪያ አፍሪካዊ ሀገር እንድትሆን አስችሏታል። የአራት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ጀርመን በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኩራሳኦን 7 ለ 1 ረምርማለች። ጀርመን ጨዋታውን የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት ብታገኝም ኮትዲቯር ጠንካራ ፉክክር ታደርጋለች ተብሎ ይጠበቃል። አሸናፊ ቡድን ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ያረጋግጣል። በዚሁ ምድብ ኢኳዶር ከኩራሳኦ በካንሳስ ሲቲ ስታዲየም ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በመጀመሪያ ጨዋታቸው ሽንፈት ያስተናገዱት ሁለቱ ሀገራት ድል ለማስመዝገብ ይጫወታሉ። በተያያዘም የምድብ ስድስት ሁለተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ። ኔዘርላንድስ ከስዊድን ከምሽቱ ሁለት ሰዓት በሂውስተን ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በመጀመሪያ ጨዋታ ኔዘርላንድስ ከጃፓን ጋር ሁለት አቻ ስትለያይ ስዊድን ቱኒዚያን 5 ለ 1 አሸንፋለች። ኔዘርላንድስ ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት እድሏን ለማስፋት ማሸነፍ ይጠበቅባታል። ተጋጣሚዋ ስዊድን ካሸነፈች ወደ ጥሎ ማለፍ ትገባለች። በዚሁ ምድብ ቱኒዚያ ከጃፓን ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ላይ በሞንቴሬይ ስታዲየም ይጫወታሉ። በመጀመሪያ ጨዋታው ሽንፈት ያስተናገደችው ቱኒዚያ በውድድሩ ላይ ለመቆየት ጨዋታውን ማሸነፍ ግድ ይላታል። አንድ ነጥብ ያላት ጃፓን ማሸነፍ ጥሎ ማለፍ የመግባት እድሏን ያሰፋላታል።
አካባቢ ጥበቃ
በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በማስተሳሰር መጪው ትውልድን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተግባራዊ ይደረጋል
Jun 20, 2026 245
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በማስተሳሰር መጪውን ትውልድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እስካሁን የተካሄዱ ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።   ከምልከታው በኋላም ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በክልሉ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ የተለያዩ ፍራፍሬ እና የደን ችግኞች ለተከላ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሚተከሉ ችግኞችም በምግብ ራስን ለመቻል የሚያግዙ እና ለእንስሳት መኖነት የሚውሉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።   የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በማስተሳሰር መጪውን ትውልድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም ነው የገለጹት።
በዞኑ የጎርፍ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የጎርፍ መከላከያ ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው
Jun 20, 2026 261
ደብረ ማርቆስ ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ጎጃም ዞን የጎርፍ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የጎርፍ መከላከያ ስራዎች በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ተጠሪ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የተጠሪ ጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ተሾመ መኮንን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ክረምትን ተከትሎ ለጎርፍ ተጋላጭ የሆኑ ስፍራዎችን በጥናት በመለየት የመከላከል ተግባሩ በቅንጅት እየተከናወነ ነው።   በጥናቱም የአባይ ሸለቆን ተከትሎ የሚገኙ ወረዳዎች ለክረምት ጎርፍ አደጋ ተጋላጭ በመሆናቸው አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ የጎርፍ መከላከያ ስራዎች በመስራት የህዝብ መፈናቀልና የንብረት ውድመት ለማስቀረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በተጋላጭነት በተለዩ የሸበል በረንታ፣ እንብሴ ሳርምድር፣ ጎንቻ ሲሶ እነሴ፣ ደጀን፣ ባሶ ሊበን፣ ስናንና የአዋበል ወረዳዎች መሆኑን አስረድተዋል። እስከ ክረምቱ መግቢያ ድረስ በሚሰራው የጎርፍ መከላከል ስራ ከ55 ሺህ በላይ ሰዎችን ለመታደግ ታልሞ እየተከናወነ መሆኑ አመልክተዋል። በጎርፍ መከላከያ ስራዎቹም ከ46 ኪሎ ሜትር በላይ ጎርፍ መቀልበሻ ቦይ፣ 6 ሺህ 800 ሄክታር መሬት ላይ የእርከን ስራ፣ ከ110 ሺህ ሜትር በላይ የማፋሰሻ ቦይ ግንባታና ክትር መሰራቱን ገልጸዋል። ለጎርፍ መከላከያ ስራዎቹ ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በጉልበትና በቁሳቁስ ከ51 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።   በዞኑ የአዋበል ወረዳ የጀር ገብርኤል ቀበሌ ነዋሪ አቶ የቆየ ደጉ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት የክረምት ወቅት የጎርፍ አደጋን መከላከል ስራ ባለመሰራቱ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ እየተከሰተ ሰብላቸውን ከጥቅም ውጭ ያደርግባቸው እንደነበር አስታውሰዋል። ዘንድሮ ይህንን ችግር ለመቋቋም በባለሙያዎች ምክረ ሃሳብና ድጋፍ በመታገዝ የእርከን፣ የጎርፍ መከላከል ስራ መስራታቸውን አስረድተዋል። የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ አንችናሉ ደሱ በበኩላቸው፤ ባለፈው ዓመት በጎርፍ ምክንያት የዘሩት የስንዴ ሰብል ከጥቅም ውጭ መሆኑን አውስተዋል። ዘንድሮ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከበጋው ጀምሮ እስካሁን ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር የጎርፍ መከላከያና መቀልበሻ ስራዎችን እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባን ጽዱ ፣ምቹ እና ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ ሕዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን አስገኝተዋል
Jun 20, 2026 270
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦አዲስ አበባን ጽዱ ፣ምቹ እና ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ ሕዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች ማስገኘታቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የጽዳት ንቅናቄ መርሃ ግብርን በይፋ አስጀምረዋል።   በንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የመዲናዋ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አዲስ አበባን ጽዱ፣ ምቹና ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ ሕዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች አምጥተዋል። አዲስ አበባን በአፍሪካ ጽዱ ከሆኑ አሥር ከተሞች አንዷ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው፣ ይሄንን ውጤት ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ ለማድረግ የሕዝቡ ርብርብ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።   ጽዳት ከአካባቢ ውበት ባሻገር ለጤና መጠበቅ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን ጠቁመው፣ ኅብረተሰቡ ጽዳትን ባህል ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። "ዛሬ በይፋ ያስጀመርነው የጽዳት ንቅናቄ ውጤታማ እንዲሆን በየብሎኩና በየአካባቢው የዕለት ተዕለት ተግባር ሊሆን ይገባል" ብለዋል። ደረጃውን የጠበቀ የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት ለመዘርጋት የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉም ብለዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው፤ ከሚወገደው ቆሻሻ ሀብት የማፍራት ሥራው ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀይሰው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።   በከተማዋ የሚመነጩ ቆሻሻዎችን ወደ ኮምፖስት ማዳበሪያ በመቀየር ለከተማ ግብርና ግብዓት እንዲሆኑ እየተደረገ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። ከፍተኛ የቆሻሻ ክምችት ባለባቸው አካባቢዎችና በሁሉም ወረዳዎች የጽዳት ቅብብሎሽና ማቀነባበሪያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የአረንጓዴ አሻራ የግብርና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ለብዝሃ ሕይወት ጥበቃና ለአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት ትልቅ አቅም ፈጥሯል
Jun 19, 2026 857
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12 /2018 (ኢዜአ):- የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የግብርና ምርታማነትን ከመጨመር ባለፈ ለብዝሃ ሕይወት ጥበቃና ለአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት ትልቅ አቅም መፍጠሩን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እስካሁን በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች በተሳካ ሁኔታ ተተክለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ2018 ዓ.ም የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን፣ በዘንድሮው ዓመት ብቻ ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታላቅ ግብ ተቀምጦ ወደ ተግባር መገባቱ ይታወቃል። ይህ ንቅናቄ ችግኞችን ከመትከል ባለፈ፣ አገራዊ መልክዓ-ምድርንና የማኅበረሰብ ሕይወትን በመቀየር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።   በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈጻሚና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የቴክኒክ ኮሚቴ ጸሐፊ ፋኖሴ መኮንን እንደገለጹት፤ መንግሥት የተፈጥሮ ሀብቶችን በዘላቂነት ለማልማትና ለመንከባከብ ኅብረተሰቡን ያሳተፈ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በስኬት ሲያከናውን ቆይቷል። ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የችግኝ ተከላ ተግባር 40 በመቶ የሚሆኑት ሀገር በቀል የደን ዝርያዎች ሲሆኑ፣ 60 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ እንደ ፍራፍሬ፣ ቡና፣ የእንስሳት መኖ፣ ለአፈር ጤንነትና ለምነት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ናቸው ብለዋል። መርሃ ግብሩ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደግ ማስቻሉን ጠቅሰዋል። ከተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ጋር ተቀናጅቶ መከናወኑም የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና ከአየር ንብረት ለውጥ መዛባት ጋር ተያይዘው የሚመጡ የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመቀነስ ጉልህ ድርሻ አበርክቷል ብለዋል። ይህም የግብርና ምርትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አቅም መፍጠሩን አስረድተዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት የደንና የግጦሽ መሬት ዕጽዋት ብዝሃ ሕይወት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበራ ስዩም በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ሀገር በቀል ዕጽዋት መልሰው እንዲያንሰራሩ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ ይህ አገራዊ ተግባር በሀገሪቱ ተስማሚና ምቹ የአየር ሁኔታ እንዲኖር በማድረግ፣ በየአካባቢው ባሉ ሥርዓተ-ምህዳሮች ውስጥ የደን ሽፋን እንዲጨምርና የብዝሃ ሕይወት ሀብቶች በአግባቡ እንዲጠበቁ ማስቻሉን አብራርተዋል። መሪ ሥራ አስፈጻሚዎቹ እንዳሉት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከሀገር ውስጥ ሁለንተናዊ ጥቅሙ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤትና ከዓለም አቀፍ ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጎለብት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። ይህ አኩሪ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ በ"አረንጓዴ ዲፕሎማሲ" በበጎ እንድትነሳ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 10076
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 7689
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 6509
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 6412
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
 የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jun 15, 2026 2099
በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉የተራሮች ስር ፈርጥ - ወልዲያ የዛሬው የወፍ በረር ምልከታችን የሚጀምረው የተራሮች ስር ፈርጥ በሆነችው ወልዲያ ከተማ በመገኘት ነው። ከደሴ በ120 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውና በረጃጅም ተራሮች የተከበበችው ወልዲያ ከተማ ከነበረችበት ጉስቁልና ወጥታ አሁን ላይ በውበት ፈክታ ትገኛለች። በሳምንቱ በዚህች ከተማ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኮሪደር ልማቷንና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፤ ተዘዋውረውም ጎብኝተዋል። በተለያዩ ታሪካዊና ባህላዊ ትውፊቶች ስሟ ጎልቶ የሚጠራው ወልዲያ እንደ ከዋክብት ፈክታ እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር እየተስፋፉ መሆኑን አንስተው በቀጣይ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ትገሰግሳለች ብለዋል። 👉የሸደር አዳሪ ትምህርት ቤት የሚቀጥለው መዳረሻችን በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን አውበሬ ወረዳ ሼደር ከተማ አዲስ የተገነባውን አዳሪ ትምህርት ቤት መመረቅ ይሆኗል። የትምህርት ቤቱን ግንባታ መርቀው ስራ ያስጀመሩት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ናቸው። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው፤ በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋት የተማረ ትውልድ ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በ138 ሚሊየን ብር የተገነባው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ስራ መጀመሩ ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል። 👉የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የበረራ ቅኝታችን ቀጥሎ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በመስኖ እየለማ ያለ የስንዴ ምርት የመጎብኘት እድል አግኝተናል። በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል መሰብሰብ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። የግብርና ሜካናይዜሽንን በስፋት በመጠቀም እንዲሁም ፈጠራን በማከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ጥረቱ በተሳካ መልኩ መቀጠሉን አንስተዋል። 👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ዓለም አቀፍ ክስተት ነው። ችግሩ በተለይም በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ ይገኛል። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መጠን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ መፍትሄ ለመስጠት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። በዚህ ረገድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት በሚከናወኑ ሥራዎች በምርምር እያገዙ ናቸው። በሂደቱ ውጤታማነት ላይ የሚመክር መድረክ በሰመራ በተደረገበት ወቅት የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ችግሩን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት በምርምርና በማማከር እያገዙ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሰዎች ህገወጥ ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ለህብረተሰቡ እየሰጡ ናቸው። 👉የኢትዮጵያ እያመረተች ነው በአማራ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እና ሌሎችም በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለውጭ ምንዛሬ አይነተኛ የገቢ ምንጭ መሆን አስችሏል ብለዋል። 👉መሶብ በአርባ ምንጭ፣ ዲላ እና ነቀምቴ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት በዚህ ሳምንት አርባ ምንጭ፣ እና ዲላ ከተሞች ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። የመሶብ ማእከላቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል። የዲጅታል አሰራርን በማስፋት ለዜጎች ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። 👉ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩ ስለመሆኑ ያነሳል። በመሆኑም ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን አደራጅቷል። በመሆኑም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በእለቱ ድምፅ መስጠት ካልቻሉት መካከል የሰሜን ምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በፊት ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፃቸውን ሰጥተዋል። በተመሳሳይ በአፋር ክልል እና በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያዎች የሚገኙ ዜጎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል። 👉የመኸር እርሻ ንቅናቄ በሲዳማ ክልል የመኸር እርሻን በንቅናቄ በመምራት የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡና ገበያን የሚያረጋጉ የግብርና ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በንቅናቄ መድረኩ ርእሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት መሬት ጦሙን እንዳያድርና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ እንዲሁም ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠት ምርታማነቱን ማሳካት አስችሏል። ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል የበልግ ሰብልን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። ይህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ በማምረት ገበያን ለማረጋጋትና ለኢንደስትሪዎች ግብአት ለማቅረብ ያስችላል ነው የተባለው። በምርት ዘመኑ የተያዘውን እቅድ ለማሳካትም አመራሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር ለውጤቱ መትጋት እንዳለበትም በውይይቱ ተነስቷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምርጥ ዘር ብዜትን በዓይነት፣ በመጠንና በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ ተችሏል። ቢሮው በግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ እና በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዘር ብዜት ዕቅድ አፈጻጸምና ዝግጅት ላይ ያተኮረ የባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ እንደገለጹት፤ በክልሉ የምርጥ ዘርን በጥራትና በመጠን ለአርሶ አደሩ በወቅቱ በማድረስ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል። ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ለኢንዱስትሪዎች በቂ ግብዓትን ለማቅረብና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር አግዟል። ተግባሩን በማስቀጠልም በ2017/18 የምርት ዘመን በክልሉ ከ2 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ30 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ማምረት መቻሉንም ገልጸዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት
Jun 14, 2026 1566
በኢዜአ ዐይን …! በሙሴ መለሰ አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው።በዚህ ሂደት ደግሞ የኢትዮጵያ ድንቅ ስራ የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊትአውራሪነት ይጠቀሳል። መርሐ-ግብሩ የጋራ ነው በሚል ዕሳቤ በርካቶችን በንቃት አሳትፎ ለዓለም የሚደርስ የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ዐሳይቷል። የደን ሽፋን መጠንን አሳድጓል። ይህም በዓየር ንብረት ለውጥ ላይ የራሱን ሚና እያበረከተ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአረንጓዴ ዐሻራ ሚና ልቆ ይነሳል። ይህም የተራቆተ መሬትን ወደ ነበረበት ከመመለስ፣ የውኃ ሀብት አሥተዳደርን ምቹ ከማድረግ እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ጋር የሚያያዝ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብሩ በዕድሜ፣ በጾታ፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሥራ ዘርፎች፣ በኑሮ ደረጃ፣ በሐይማኖት ሳትለይ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች እንዲሳተፉበት በማድረጓ በዘርፉ ስኬታማ ጉዞ ላይ ናት። ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀት ከመሆን አልፎ ለጎረቤቶቿ ችግኝ በመለገስ መርሐ-ግብሩ እንዲስፋፋ እየተጋችም ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ሲናገሩ፤ አረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያ ትላልቅ ነገር አስባ፣ ትላልቅ ነገር ተልማ፣ ትላልቅ ነገር አቅዳ እና ሕዝቦቿን አስተባብራ ማሳካት እንደምትችል ለሌሎቹ ማሳያ ነው ማለታቸውም ከላይ ያነሳነውን ሐሳብ ያዳብረዋል። በተጨማሪም አረንጓዴ ዐሻራ በልዩ ትኩረት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሳይቆራረጥ እየተሠራ መሆኑን፤ በየዓመቱም በሚተከሉ ችግኞች ብዛት፣ በሚተከልበት መሬት ስፋት እና በሚሳተፉ ታታሪዎች ቁጥር እያደገ መሆኑን ያመላክታል። በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች እየወጡ በችግኝ ተከላ መሳተፋቸው የሀገርን የጋራ ራዕይ ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 6165
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም
Jun 5, 2026 11956
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰርን ለመከላከል ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች በወቅቱ ካልታከመ ለኩላሊት መድከም፣ ለደም መመረዝና ለሞት የሚያደርሰው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
ትንታኔዎች
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 2133
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ።   ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…! 
Jun 15, 2026 1306
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 6165
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው?
Jun 12, 2026 2286
የጤና ነገር … በዮሐንስ ደርበው የሰው ልጅ ሊሻሻሉ በሚችሉ እና በማይችሉ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ለልብ ህመም ሊጋለጥ እንደሚችል የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የአዋቂ የልብ ሕክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ብርሃኑ ሞገስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የልብ ህመም ከተወሳሰብ ዘላቂ የጤና እክል እስከ ድንገተኛ ኅልፈት ያደርሳል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ሰዎች ማሻሻል በሚችሏቸው (ሞዲፋይብል) እና ማሻሻል በማይችሏቸው (ነን ሞዲፋይብል ወይም ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች) ለልብ ህመም ሊጋለጡ እንደሚችሉ ዶክተር ብርሃኑ ይገልጻሉ። መሻሻል ከሚችሉ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል፤ ከፍተኛ ጭንቀት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ ከፍተኛ የደም ግፊት ህመም (በአግባቡ መድኃኒቱ ካልተወሰደ)፣ተገቢ ያልሆነ የስብ ክምችት፣ ከፍተኛ ውፍረት (ክብደት)፣ በቂ እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ጤናማ አመጋገብ አለመኖር እንዲሁም አብዝቶ ስኳር፣ ጣፋጭና አልኮል መጠቀም የሚሉትን ይጠቅሳሉ፡፡ እንዲሁም ሰዎች ማሻሻል ከማይችሏቸው (ተፈጥሯዊ) አጋላጮች መካከል፤ በቤተሰብ የሚተላለፍ መኖሩን፣ በዕድሜ መጨመር የሚከሰት መሆኑን (ለምሳሌ፡- ወንድ ከ45 ሴት ከ55 ዓመት በላይ ሲሆናቸው ለልብ ህመም ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩን) እንዲሁም ወንዶ ከሴቶች በይበልጥ ለልብ ህመም ተጋላጭ የመሆናቸው አጋጣሚ ሰፊ ሊሆን እንደሚችልም አብራርተዋል፡፡ በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የልብ ህመም ምልክቶች የደረት ውጋት በግራ በኩል ወይም መሐል ላይ፣ ከወትሮው የተለየ ድካም፣ ትንፋሽ ማጠር፣ ከመደበኛው የተለየ የልብ ምት መኖር፣ የሰውነት በተለይም እግር አካባቢ እብጠት፣ ራስን መሳት እና ሳል የልብና ተያያዥ ህመም ምልክት ሊሆኑ እንደሚችሉ አብራርተዋል። የልብን ጤናን ለመጠበቅ በተቻለ መጠን ጤናማ አመጋገብን መከተል እንደሚገባ የሚመክሩት ዶክተር ብርሃኑ፤ አትክልት ማዘውተር፣ ምግብ ሲዘጋጅም ፈሳሽ ዘይት መጠቀም፣ ስኳር፣ ጨው እና ጣፋጭ ነገሮችን መገደብ ከተቻለም ማስወገድ እንደሚገባ ይመክራሉ፡፡ አካላዊ እንቅስቃሴ ማዘውተር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ይህም ብስክሌት መንዳት፣ በእግር እንቅስቃሴ ማድረግ፣ ዋና መዋኘት፣ እስከሚያልብ እና የልብ ምት እስከሚጨምር ብሎም እስከሚደክሙ የአካል ብቃት መሥራት የልብን ጤና ለመጠበቅ አስተዋጽዖ አለው ነው ያሉት፡፡ ጤናማ የሰውነት ክብደት እንዲኖር ማድረግ ተገቢ መሆኑን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ “ቦዲ ማስ ኢንዴክስ (ቢ ኤም አይ)” ከ18 ነጥብ 5 እስከ 25 እንዲሆን ይመከራል ብለዋል፡፡ ሲጋራ አለማጨስ፣ አልኮል አለመጠቀም፣ የስኳር ህመምና ከፍተኛ ደም ግፊት ካለም የመድኃኒት አወሳሰድን አለማስተጓጎል፣ አመጋገብ ላይ ስብ አለማብዛትና አብዝቶ አለመቀመጥ የልብ ህመምን ለመከላከል እንደሚያግዙ ነው ያስረዱት፡፡ ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በታች የሆኑ ጤናማ ሰዎች ከአንድ እስከ ሦስት ዓመት ባሉ ጊዜያት አንድ ጊዜ፣ ዕድሜያቸው ከ45 በላይ የሆኑ በየዓመቱ እንዲሁም የልብ ህመም ያለባቸው እንደሁኔታው በየጊዜው ክትትል እንዲያደርጉም መክረዋል፡፡ ሰዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እራሳቸውን ከልብ ህመም እንዲጠብቁ መክረው፤ ከዚህ ያለፈ ችግር ሲኖር ቶሎ የሕክምና ክትትል ማድረግ እና “ዛሬ ነገ” በማለት ጊዜ እያባከኑ ህመሙ ውስብስብ ደረጃ እስኪደርስ መጠበቅ እንደማይገባቸው አሳስበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ጤና #የልብ_ህመም
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 1349
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 15952
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 9036
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 14804
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 84858
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 67135
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 47472
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 45043
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 34114
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 33600
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 33062
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 32310
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 84858
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 67135
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 47472
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 45043
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም
Jun 5, 2026 11956
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰርን ለመከላከል ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች በወቅቱ ካልታከመ ለኩላሊት መድከም፣ ለደም መመረዝና ለሞት የሚያደርሰው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 7885
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም