ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ነገሌ አርሲ እና ምድረ ገነት ሽሬ ነጥብ ተጋሩ
May 21, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 33ኛ ሳምንት ነገሌ አርሲ እና ምድረ ገነት ሽሬ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ተካሄዷል። ጨዋታውን ተከትሎ ነገሌ አርሲ በ52 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ነገሌ አርሲ የሁለተኝነት ደረጃን ከመቻል የመረከብ እና ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት የማጥበብ እድል አልተቀመበትም። ምድረ ገነት ሽሬ በ37 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ዛሬ አስቀድመው በተደረጉ የ33ኛ ሳምንት ጨዋታዎች የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና አርባምንጭ ከተማን 3 ለ 0 ሲረታ አዳማ ከተማ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 33ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ከኢትዮጵያ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች በኋላ ከግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
በክልሉ ለአምራች ኢንዱስትሪው በተሰጠ ትኩረት በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር እያደገ መጥቷል - አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
May 21, 2026 110
ሀዋሳ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ለአምራች ኢንዱስትሪው በተሰጠ ትኩረት በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር እያደገ መምጣቱን የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። በሀዋሳ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ዛሬ ተመርቋል። የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ እንዳሉት እንደ ሀገር በተፈጠረው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ በአምራች ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት ታይቷል። ለአምራች ኢንዱስትሪው በተሰጠው ልዩ ትኩረትም በክልሉ በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር እያደገ መምጣቱ ተናግረዋል። አምራች ዘርፉ ከፍተኛ የሰው ሃይል የሚፈልግ በመሆኑ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል። ከአነስተኛ ወደ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ማደግ እንደሚቻል አበባ ጨርቃ ጨርቅና ቆዳ ስፌት አክሲዮን ማህበር ያስገነባው የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ አንድ ማሳያ ነው ብለዋል። የክልሉ አንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበሩ በበኩላቸው መንግስት አምራች ኢንዱስትሪውን በማበረታታት በርካቶችን ወደ ሥራ እንዲገቡ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ በክልሉ የተለያዩ ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪው መስክ እንዲሰማሩ ለማበረታታትም በዘርፉ ለሚሰማሩ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው ምቹ ቦታዎችን ማዘጋጀቱንም ተናግረዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ አገና ኔቶ እንዳሉት በከተማዋ ከ1 ሺህ በላይ አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ይገኛሉ። ኢንዱስትሪዎቹ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡትን በማምረት በኢኮኖሚው ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆናቸውንም አስታውቀዋል። የአበባ ጨርቃ ጨርቅና ቆዳ ስፌት አክሲዮን ማህበር ሥራ አስኪያጅ ወሌ አበጋዝ (ዶ/ር) በበኩላቸው ለፋብሪካው ግንባታ ከ582 ሚሊዮን በር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት ፋብሪካው ለ153 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል መፍጠሩን ገልጸው፣ በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባ ለ310 ሰዎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በመታገዝ ወደ ኤክስፖርት ምርት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፣ ጥራት ያለው ምርት ለማምረትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በፋብሪካው የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል ወጣት ኤደን ዘርፉ እንዳለችው በፋሽን ዲዛይን ትምህርት መስክ ተመርቃ በፋብሪካው መቀጠሯን ተናግራለች።
በክልሉ በግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ወጣቶችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ላይ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ
May 21, 2026 64
ሀዋሳ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ወጣቶችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ላይ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለፀ፡፡ በሲዳማ ክልል የእርሻውን ዘርፍ ለማዘመንና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት በማለም የእርሻ ትራክተሮችን በዘርፉ ለተደራጁ ወጣቶች የማስረከብ መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡ በዚህ ወቅት የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ እንዳሉት፤ በክልሉ እየተከናወኑ ባሉ የግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ሥራዎች ወጣቶችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ ይገኛል። የግብርና እና ገጠር ትራንፎርሜሽንን ለማረጋገጥ ግቦች ተጥለው ማሳካት የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የምግብና ሥነ ምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ፣ ለገበያ የማምረት፣ ኤክስፖርትን የማሳደግና ገቢ ምርትን የመተካት እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ የግብርና ምርቶችን በስፋት የማምረት ግቦች እንዳሉ ጠቅሰዋል፡፡ በግብርና ዘርፍ ለተደራጁ ወጣቶች የእርሻ ትራክተሮች ርክክብ መከናወኑን ገልፀው በዚህም በአጠቃላይ 148 ወጣቶች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አስረድተዋል፡፡ የአካታችና ዘላቂ የግብርና እሴት ሰንሰለት ልማት ፕሮጀክት ብሔራዊ አስተባባሪ ሰለሞን ዳኜ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በገጠር በተለይ ወጣቶችና ሴቶችን አደራጅቶ ተሳታፊ በማድረግ የገጠሩን ኢኮኖሚ የማሳደግ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በመሆኑም ምርትና ምርታማነትን በማስፋትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት በኩል ፕሮጀክቱ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ትራክተሮቹን ከተረከቡ ማህበራት መካከል የቦና ወረዳ ወጣት ንግስት አምሳለ ማህበራቸው በቆሎ፣ ስንዴ እንዲሁም አቮካዶ፣ ማንጎና ሌሎች የተለያዩ ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ፍራፍሬዎችን እንደሚያመርት ገልፃለች፡፡ ከዚህ ቀደም የግብርና ሥራውን ባህላዊ በሆነ መንገድ ስለሚያከናውኑ ውጤታማነታቸው እምብዛም እንደነበር ገልፃ አሁን ላይ ሰፊ መሬትን በትራክተር በተሻለ ሁኔታ በማረስ ተጠቃሚ የሚያደርጋቸውን ዕድል እንዳገኙ ተናግራለች፡፡ የዳራ ወረዳ ወጣት አዲሱ ሌላሞ በበኩሉ ማህበራቸውም ሆነ በአካባቢያቸው ያሉ አርሶ አደሮች በበሬ አልያም በጉልበት የእርሻ ሥራቸውን እንደሚያከናውኑ ተናግሯል፡፡ ትራክተሮቹን የራሳቸውን እንዲሁም በአካባቢያቸው ያሉ አርሶ አደሮችን ማሳ ለማረስ እንደሚጠቀሙባቸው ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልፅግና በልጆቿ ጥረት ዕውን ማድረግ እንደሚቻል የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ ህያው ምስክር ነው
May 21, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልፅግና በልጆቿ ጥረት ዕውን ማድረግ እንደሚቻል የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ ህያው ምስክር መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኩን የጎበኙ የመዲናዋ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ግንቦት 8 ቀን 2018 የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን መርቀው ሥራ ማስጀመራቸው ይታወቃል። ከአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎችም የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የልማት ውጤትና የአምራቾችን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት የተጠሪ ተቋማት ዘርፍ ኃላፊ ዳዲ ወዳጆ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኢንዱስትሪ ክላስተር መሆኑን ገልጸዋል። የኢንዱስትሪ ፓርኩም የአምራቾችን ዓለም አቀፍ የተወዳዳሪነት አቅም በመገንባት ሀገራዊ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት ገንቢ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ለዚህም ፓርኩ የአዲስ አበባና የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥን የኢንዱስትሪ ምርታማነትን ምኅዳር እንደፈጠረ አንስተዋል። አዲስ አበባ በሁሉም ዘርፍ ስኬታማና ውጤታማ የልማት ሥራዎችን ዕውን የምታደርግ ከተማ መሆኗን የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ እንደሚያሳይ አስረድተዋል። የኢንዱስትሪ ፓርኩም ለመካከለኛና ከፍተኛ አምራቾች ምቹ የሥራ ከባቢ በመፍጠር በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በተኪና ወጪ ንግድ የምርት አቅም መገንባት የሚያስችላቸው መሆኑን አብራርተዋል። ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የመጣው አብዱራሂም አስገዶም፤ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ኢትዮጵያዊያን መስራትና ለውጥን ማምጣት እንደሚችሉ የሚያሳይ አስደናቂ የልማት ውጤት ነው ብሏል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልፅግና በልጆቿ ጥረት ዕውን ማድረግ እንደሚቻል የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ ህያው ምስክር መሆኑን ተናግሯል። ሌላኛው ከለሚኩራ የመጣው አስቻለው ሙሉጌታ በበኩሉ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ አምራቾች የሚገጥማቸውን የመስሪያ ቦታ ችግር የሚቀርፍ የልማት አቅም መሆኑን ገልጿል። የጉለሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪዋ የጉብኝቱ ተሳታፊ ፍጹም አምሳሉ፤ የኢንዱስትሪ ፓርኩ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት አቅም የሚሆን የማምረቻ ከባቢ መሆኑን ተናግራለች። የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ በርካታ የመዲናዋ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ አስደናቂ ፕሮጀክት ነው ያለው ደግሞ ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ የመጣው ዮኃንስ ሰለሞን ነው። ፓርኩም የተኪ ምርታማነትን በማሳደግ ለሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ገበያ መቅረብ የሚችሉ የኢንዱስትሪ ምርቶችን የማምረት አቅም እንደሚያጎለብት ማየቱን ተናግሯል።
መንግስት ለህዝብ የገባውን ቃል ይፈፅማል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
May 21, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት ለህዝብ የማይሰራውን ቃል አይገባም፤ ለህዝብ የገባውን ቃል ይፈፅማል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬም የኑሮ ውድነትን ለማቃለል፣ ምርት በብዛት ማቅረቢያ እና የግብይት ማዕከላት የማስፋት ስራችን አካል የሆነው 7ኛውን የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከልን ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል ብለዋል። ማዕከሉ የኑሮ ውድነትን የሚያቃልሉ ዘመናዊ፣ ማሞቂያ እና ማቀዝቀዣ ያላቸው 221 መጋዘኞች፥ የችርቻሮ ሱቆች፥ ሱፐር ማርኬቶች፣ ወፍጮ ቤቶች፣ በአንድ ጊዜ 250 ተሽከርካሪዎችን ማቆም የሚችል ፓርኪንግ፣ ለለሚ ኩራ፣ ለቦሌ እና የካ ክፍለ ከተሞች ነዋሪዎች በአማካይ ቦታ እና ሰሚት ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ምቹ የሆነ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ነው ብለዋል። በገበያ ማዕከሉ ማህበረሰቡ ለዕለት ፍጆታ የሚጠቀምባቸውን የሰብል ምርቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬዎች፣ የበርበሬ ፣የቅመማቅመም ምርቶች እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን የአንድ ማዕከል የግብይት ስርዓትን እውን ማድረግ መቻሉን ነው ከንቲባዋ የገለጹት። በማዕከሉ የሚቀርቡ ምርቶች ከ15 እስከ 20 በመቶ የዋጋ ቅናሽ የሚሸጥበት፥ ዋጋ የሚያንረውን ህገ-ወጥ የደላላ ሰንሰለት በመበጣጠስ ከአምራቹ ያልተቋረጠ ምርት የሚቀርብበትና የከተማዋ ነዋሪዎችን የኑሮ ጫና እንደሚያቃልል አመልክተዋል። በገበያ ማዕከሉ ከተለያየ ቦታ በኮሪደር ልማት የተነሱ ነዋሪዎችን ጨምሮ ማዕከሉ ያረፈበትን 3 ነጥብ 2 ሄክታር መሬት ለልማት የለቀቁ አርሶ አደሮችም ሱቅ እንዲያገኙ መደረጉንና በዚህም ለነዋሪዎች ሰፊ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር እንዲሳካ ጥረት ላደረጉ የዲዛይንና የኮንስትሪክሽን ስራዎች ቢሮ አመራርና ሰራተኞች፣ የንግድ ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች፣ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አመራሮች፣ ቦታው ለልማት እንዲውል ለሰጣችሁ አርሶ አደሮች በራሴና እና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመሰግናለሁ ብለዋል።
ፖለቲካ
ፓርቲው በሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚ አድርጓል
May 21, 2026 178
ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ባከናወናቸው ሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን የገንዳውኃ፣ ሰቆጣ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃንና ኮምበልቻ ከተሞች አስተያየታቸውን የሰጡ ሴቶችና ወጣቶች ገለጹ። በገንዳውኃ፣ ሰቆጣ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃንና ኮምቦልቻ ከተሞች “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!" በሚል መሪ ሐሳብ የቅስቀሳና ድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይ ከተሳተፉት መካከል ወይዘሮ የምስራች አበበ እንዳሉት፤ ፓርቲው ሴቶች ተደራጅተው መብትና ጥቅማቸውን እንዲያስጠብቁ አድርጓል ብለዋል። ሴቶችን ወደ አመራር በማምጣት፣ በተለያዩ ገቢ ማስገኛ ስራዎች እንዲሰማሩ በመደገፍና በልማት ስራዎች በማሳተፍ ኑሯቸውን እንዲቀይሩ ማድረጉን ገልጸዋል። ሌላዋ የድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊ ቤዛዊት አስናቀው ኢትዮጵያን በምግብ ራሷን በማስቻል ወደ ተሻለ እድገት ለማሻገር የተሰራው ስራ ፍሬ ማፍራቱን ጠቁመዋል። በብልጽግና ፓርቲ የገንዳውኃ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አስማረች ቆያቸው ፓርቲው የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በሰቆጣ ከተማ በተካሄደው ሰልፍ ላይ የተገኙት የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንታይቱ ካሴ እንደገለጹት ብልፅግና የህብረ ብሔራዊ አንድነትና የአብሮነት ተምሳሌት ነው ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ላቀች ሰማ እንዳሉት መንግስት ባለፉት ዓመታት ሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት ሰርቷል። በቀጣይም ሴቶችን በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች የላቀ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ እንደሚሰራ ገልጸዋል። ወይዘሮ ሰላም ተመስገን እና ወይዘሮ እመቤት አንዷለም እንዳሉት ፓርቲው የያዘውን ራእይ ለማሳካት የድርሻችን እንወጣለን ብለዋል። እንዲሁም በደብረ ብርሃን ከተማ የድጋፍ ሰልፍ ተሳታፊ የሆኑት ወይዘሮ አባይነሽ ሃይሉና ወይዘሮ ረድኤት በሻው እንደገለጹት ፓርቲው የጀመራቸውን የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደትን ከዳር ለማድረስ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወይዘሮ ዓለም መኩሪያ እንደገለጹት ፓርቲው ሴቶችና ወጣቶችን በማሳተፍ እየሰራ ይገኛል። በፓርቲው የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሙሉጌታ አቢ በከተማዋ በተካሄደው ሰልፍ ላይ እንደገለጹት ፓርቲው የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ መጪውን ትውልድ ለመገንባት አልሞ እየሰራ ይገኛል።
በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት በፈፀምነው ጥፋት በመጸጸት የልማት አርበኛ ለመሆን ተዘጋጅተናል-የቀድሞ ታጣቂዎች
May 21, 2026 208
ኮምቦልቻ፤ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት በፈፀምነው ጥፋት በመጸጸት የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር ለመሆን ተዘጋጅተናል ሲሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በአማራ ክልል ጫካ ገብተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል በኮምቦልቻ የተሃድሶ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት በፈፀምነው ጥፋት በመጸጸት የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር በመሆን ህዝብን ለመካስ ተዘጋጅተናል ብለዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አሸናፊ ደሳለኝ፥ ህዝቡ የሚፈልገው ሰላምና ልማት መሆኑን በተግባር አሳይቶናል ሲል ተናግሯል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት ህዝብን ለእንግልት፣ዘረፋና ችግር ዳርገናል ነው ያለው። በዚህም የመንግስትን ጥሪ ተቀብለን ሰላምን በማስከበርና ልማትን በመደገፍ ለመካስ ተዘጋጅተናል ብሏል። ታጣቂ አለፉ ንጉሴ እና ሃምሳ አለቃ ሞላ ጎሹ በበኩላቸው፥ ለአማራ ህዝብ እንታገላለን በሚል የተሳሳተ ፕሮፓጋንዳ በርካታ ወጣቶች መታለላቸውን አንስተዋል። የህዝብን ንብረት ከማውደም፣ከመዝረፍና እገታ ውጭ ሌላ አላማ አለመኖሩንም ተናግረዋል። በርካቶች በጥፋታቸው በመጸጸት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ስለመምጣታቸውም ጠቁመዋል። የአማራ ክልል ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አማካሪ ኮሎኔል ባምላኩ አባይ፤ በክልሉ በርካታ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ በመቀበል ስልጠና እየወሰዱ ወደ ማህበረሰቡ እየተቀላቀሉ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ለሰላም በሩ ክፍት በመሆኑ ጫካ ያሉ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርበዋል። በብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የስልጠና ዳይሬክተር ብርሃኑ ተስፋዬ፤ በተለያዩ አካባቢዎች የቀድሞ ታጣቂዎችን በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና እንዲወስዱና ህብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ እየተደረገ ነው ብለዋል። የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ ህዝቡን በልማት መካስ እንዳለባቸው በማሳሰብ በቀጣይም ተመሳሳይ ስራዎች የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል።
የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም ዘብ በመሆን የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል
May 21, 2026 233
ጎንደር ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ በመሆን የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ሲሉ የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ ገለጹ። የሠላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል የጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በመገኘት የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም(ዲዲአር) ፕሮግራምን አስጀምረዋል። ሚኒስትሩ በተሃድሶ ስልጠናው ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፤ መንግስት የሠላም ጥሪውን የተቀበሉ ታጣቂዎች የሠላም አምባሳደር በመሆን ህዝባቸውን እንዲክሱ የማቋቋም ስራ እያከናወነ ነው። የቀድሞ ታጣቂዎች ሠላምን አማራጭ በማድረግ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ በመሆን የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን ፤ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ህይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል። ብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽኑ በአማራ ክልል የሠላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም ወደ ማህበረሰቡ የመቀላቀል ስራ ማከናወኑን ተናግረዋል ። በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የአስተዳደር ጉዳዮች ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር)፤ በክልሉ የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም የሠላም ዘብ ሆነው እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ክልሉ አሁን ላይ ወደ አስተማማኝ ሠላም በመሸጋገሩ በርካታ የልማት ተግባራትን ማከናወን የተቻለበት ሁኔታ መፈጠሩን አመልክተዋል። የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ በሪሁን መንግስቴ፤ የሠላምን አማራጭ በመቀበል ወደ ክልሉ የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎች የሠላም አምባሳደር በመሆን እየሠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል ። የቀድሞ ታጣቂዎች የሠላም አማራጭ መከተላቸው ለክልሉ የሠላም ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የላቀ ነው ብለዋል። የሠላም ጥሪውን ተቀብለው ከገቡ የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል ባዬ ቀናው፤ በተከተልነው የተሳሳተ መንገድ ህዝብና መንግስትን በድለናል ብሏል። የሠላም ጥሪውን የተቀበልነው ለሠላም ካለን ቁርጠኛ አቋም በመሆኑ በልማት ስራዎች በመሳተፍ ህዝብና መንግስትን ለመካስ ዝግጁ ነን ሲል አክሏል። በተሀድሶ ስልጠና ማስጀመሪያ ስነ-ስርአቱ ላይ የፌዴራል፣ የክልልና የጎንደር ከተማ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያና አሜሪካን ታሪካዊ ግንኙነት ወደላቀ አጋርነት ማሸጋገር ያስቻለ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ሥራ ተሰርቷል
May 21, 2026 206
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና አሜሪካን ታሪካዊ ግንኙነት ወደላቀ አጋርነት ማሸጋገር ያስቻለ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ሥራ መሰራቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያን የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደላቀ ምዕራፍ ያሸጋገረ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፤ በሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ የተከናወኑ ዐበይት ክንውኖችን በማስመልከት ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ ባለፈው ሳምንት በሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ የኢትዮጵያን ትብብር፣ አጋርነትና የኢንቨስትመንት ምቹነት ያረጋገጡ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል። በሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የግንኙነት መድረኮቹም ጠንካራና ንቁ ዲፕሎማሲ ተሳትፎ ማድረግ ያስቻሉ እንደነበር አስታውሰዋል። ለአብነትም በኢትዮጵያና አሜሪካ መካከል የተደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች የሀገራቱን ከ120 ዓመታት በላይ የተሻገረ ታሪካዊና ጠንካራ ወዳጅነት ዘላቂና ተቋማዊ ማድረግ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። የሀገራቱ የሁለትዮሽ መዋቅራዊ የምክክር መድረክና ስምምነትም ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትን በማጠናከር ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በሁለትዮሽ ስምምነቱም የሀገራቱን ንግድና ኢንቨስትመንት፣ የፀጥታና መከላከያ ትብብር ወደላቀ ምዕራፍ በማሸጋገር የጋራ የኢኮኖሚ ብልፅግናን ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ እንደነበር አንስተዋል። በኢትዮጵያና አሜሪካ መንግስታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተደረገው የዲፕሎማሲ ምክክርም ታሪካዊ ወዳጅነትን ወደላቀ አጋርነት ለማሸጋገር ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን አብራርተዋል። በሁለትዮሽ መድረኮቹም የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገትና ብልፅግና ሞዴል እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ገለፃ መደረጉን አስረድተዋል። የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝትም የሀገራቱን ታሪካዊ ወዳጅነት ይበልጥ የሚያጎለብት የትብብር ስምምነቶች የተፈረመበት መሆኑን ገልጸዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 80ኛ ዓመትን በማስመልከትም የኢትዮጵያን መስራችነት፣ የሰላም ማስከበር ስኬታማ ተልዕኮና የጋራ ታሪክ የሚያሳይ ልዩ የቴምብር ስብስብ ማሳተሟን ጠቅሰዋል። ይህም ኢትዮጵያ ለባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነትና ታሪካዊ ትስስር የዘከረ መሆኑን ተናግረዋል። በሕንድ በተካሄደው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባም ኢትዮጵያ ሁሉንም ሀገራት በፍትሐዊነት የሚያገለግል ሥርዓት ሊዘረጋ እንደሚገባ ያላትን አቋም ማንፀባረቋን አስረድተዋል። ከብሪክስ ስብሰባ በተጨማሪ ከአባል ሀገራቱ ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችሉ ፍሬያማ ውይይቶች መካሄዳቸውን ተናግረዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም በደቡብ አፍሪካና ሳዑዲ አረቢያ ያሉ ዜጎችን ደኅንነት ማስጠበቅ የሚያስችሉ ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። የኢትዮጵያን ፍትሐዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ታሪካዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ለማስገንዘብ የሚደረጉ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
በክልሉ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን የሚያረጋግጡ የመደመር መንግስት ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች እየተተገበሩ ነው
May 21, 2026 229
ቴፒ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን የሚያረጋግጡ የመደመር መንግስት ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች በክልሉ እየተተገበሩ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። በክልሉ ቴፒ ከተማ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ የቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የመደመር መንግስት እኩል የምንደመጥበትን ምቹ አውድ ፈጥሯል ብለዋል። በዚህም ክልሉ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት አግኝቶ ያደሩ መሠረተ ልማቶችን ከማጠናቀቅ ባለፈ አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶችን አቅዶ በመተግበር ሕዝብን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ክልሉ ያለውን ጸጋ በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማምጣትና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ላይ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በፓርቲው መሪነት የተገኙ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ትሩፋቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም በጠቅላላ ምርጫው ህዝቡ ለፓርቲው ይሁንታ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው እንዳሉት፤ ፓርቲው የሕዝቡን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሰራ ነው። የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ በመመለስ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ህብረተሰቡን በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሕዝቡ በምርጫው ዕለት በነቂስ ወጥቶ ድምጹን ለፓርቲው በመስጠት ከጎኑ እንዲሆንም ጠይቀዋል። በክልሉ መልካም እሴቶችንና ወንድማማችነትን እያጎለበተ ያለው ብልጽግና ፓርቲ በዞኑ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ አድርጓል ያሉት ደግሞ የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ናቸው። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ፍትሐዊ የመልማት ዕድል ዞኑ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱን ገልጸው፣ የአካባቢውን እምቅ የተፈጥሮ ጸጋ ወደ ኢኮኖሚ ምንጭነት ለመቀየርም በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የመጀመሪያውን የምርጫ ካርዳችንን የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት እንጠቀምበታለን
May 21, 2026 178
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የመጀመሪያውን የምርጫ ካርዳቸውን የሀገርን ልማትና ዕድገት በማፋጠን የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት እንደሚጠቀሙበት የአዲስ አበባ ወጣቶች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጡበታል ተብሎ የሚጠበቀው ጠቅላላ ምርጫ ውስን ቀናት ቀርተውታል። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባም በተለያዩ ምዕራፎች በማካሄድና በማራዘም ከየካቲት 28 እስከ ሚያዚያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ ቆይቶ ተጠናቋል። በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ከ50 ሚሊየን 514 ሺ በላይ ዜጎች ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ መውሰድ ችለዋል። በጠቅላላ ምርጫው 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ታዛቢነት ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር ውስጥ ድርጅቶችም በተለያዩ አካባቢዎች ከ60 ሺህ 277 በላይ ወኪሎችን አሰማርተዋል። በመራጮች ትምህርት ላይ ዕውቅና የተሰጣቸው 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ለመራጩ ህዝብ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርትና ስልጠና እየሰጡ ይገኛል። የአዲስ አበባ ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ጠቅላላ ምርጫው ሕገ-መንግሥታዊ የመምረጥ መመረጥ መብት በአደባባይ የሚታይበት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ልምምድ መገለጫ ነው። ለዚህም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ማዕከላት በአካልና በዲጂታል አማራጭ የምርጫ ካርድ በማውጣት ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እንዳደረጉ ገልጸዋል። በሂደቱም የሀገርን ዘላቂ ልማትና ዕድገት በማፋጠን የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ እንደሚሰጡ አረጋግጠዋል። የ12ኛ ክፍል ተማሪዋ ወጣት መቅደላዊት ሁሴን፤ ምርጫ የሕገ-መንግሥታዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ልምምድ መገለጫ ነው ብላለች። በዚህም ለመጀመሪያ ጊዜ በወሰደችው የምርጫ ካርድ የተሻለ የፖሊሲ አማራጭ ላለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገልፃለች። ወጣት ዳዊት ወንደሰን በበኩሉ፤ በምርጫ ሂደት ዜጎች የሚኖራቸው የነቃ ተሳትፎ የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለመበየን የማይተካ ሚና እንዳለው ተናግሯል። በጠቅላላ ምርጫውም ሕገ-መንግሥታዊ መብቱን በመጠቀም ድምፅ እንደሚሰጥና ለምርጫው ስኬትም ገንቢ ሚና እንደሚወጣ አረጋግጧል። ወጣት ዳግማዊት ዳንኤልም፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንደወጣት የሚጠበቅባትን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብላለች። ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎች ድምፅ ሰጥቶ እንደማያውቅ ያስታወሰው ደግሞ ወጣት ምህረቱ በቀለ ነው። በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫም ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በመውሰድ ለሀገር ዕድገትና ወጣቶች ተጠቃሚነት ይበጃል የሚለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቱን አረጋግጧል።
የህዝብን የልማት ጥያቄ የሚመልስና ሀገርን የሚያሻግር ፖሊሲ ላለው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል
May 21, 2026 202
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦የህዝብን የልማት ጥያቄ የሚመልስ እና ሀገርን የሚያሻግር ፖሊሲ ላለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የሲዳማ ክልል ነዋሪዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ ተይዟል፡፡ ቦርዱ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረትም ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ50 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የምርጫ ካርድ የወሰዱ ሲሆን፣ ዜጎቹም በካርዳቸው ይሆነኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ ናቸው። ኢዜአ ያነጋገራቸው በሲዳማ ክልል የቡራ እና በንሳ ወረዳ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ በወሰዱት ካርድ ሀገር የሚያሻግር የፖሊሲ አማራጭ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ ነው፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡት የቡራ ወረዳ ነዋሪዎች መካከል አቶ አለማየሁ አርጋታ እና አቶ አዱኛ አማቼጅ እንደገለጹት፤ በጠቅላላ ምርጫው ድምጽ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የምርጫ ካርድ በወቅቱ ወስደዋል፡፡ በድምጽ መስጫው እለትም የተሻለ የፖለሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የፓርቲዎችን የቅስቀሳና የክርክር ሂደት እየተከታተሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የበንሳ ዳዬ ከተማ ነዋሪ ወጣት ዘላለም ዘነበ፣ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለሚያረጋግጥ ፓርቲ ድምጿን ለመስጠት ተዘጋጅታለች። ወጣቶች ለሀገር ሰላምና ዴሞክራሲ ግንባታ ያላቸውን ሚና በተግባር መወጣት እንዳለባቸው ገልጻ፣ በምርጫ ቀን ዴሞክራሲያዊ መብቷን ከመጠቀም ባለፈ ሰላማዊና ፍትሀዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሏን ለመወጣት መዘጋጀቷን ተናግራለች። ለወጣቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ይበልጥ ተግቶ የሚሰራ ፓርቲን ለመምረጥም ፓርቲዎች በተለያዩ መንገዶች የሚያደርጉትን ቅስቀሳ በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን ጠቁማለች። ምርጫው ከሂደቱ ጀምሮ ሰላማዊ፣ ፍትሀዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ለመወጣት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የበንሳ ወረዳ ነዋሪ አቶ ታደሰ ጎኖሶ ናቸው። ለሀገር ቀጣይነት ያለው እድገትና ለዜጎች ተጠቃሚነት ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ወሳኝ መሆኑን ያነሱት አቶ ታደሰ በዚህ ረገድም ተከታታይ ትምህርትና ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
የምርጫ ሂደቱ ምቹ የፖለቲካ ምህዳርና አስቻይ ሁኔታዎች የተፈጠሩበት ነው- የፖለቲካ ፓርቲዎች
May 21, 2026 261
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ምቹ የፖለቲካ ምህዳርና አስቻይ ሁኔታዎች የተፈጠሩበት መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የዘንድሮው የምርጫ ሂደትና አጠቃላይ ቅንጅት ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ያስቻለ ስለመሆኑም የፓርቲ አመራሮቹ ተናግረዋል። አጠቃላይ የእስካሁኑን የምርጫ ሂደት አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ምቹ የፖለቲካ ምህዳርና አስቻይ ሁኔታዎች የተፈጠሩበት መሆኑን ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሃፊ እና የኢዜማ ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ታሪኩ ድንበሩ፤ በጋራ ምክር ቤቱም ሆነ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ለምርጫው ዴሞክራሲያዊነት እና ሰላማዊነት በትብብር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። በተለይም የጋራ ምክር ቤቱ የምርጫ እቅድ አዘጋጅቶና ኮሚቴ አዋቅሮ ወደ ስራ መግባቱን የገለጹት አቶ ታሪኩ፤ በ21 የክልሉ ዞኖች እና በ213 ወረዳዎች ምክር ቤት ተቋቁሞ የተሻለ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። በምክር ቤቱ ስር የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተሻለ መልኩ ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን፣ በሂደቱ ያጋጠሙ ችግሮችም በፍጥነት እየተፈቱ መሆኑን አረጋግጠዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በቀደሙት ምርጫዎች ወቅት እንደ ስጋት የሚታዩ ችግሮች የተቀረፉበት እና ምርጫው ሰላማዊ፣ ተአማኒ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት በጋራ እየሰሩ ያሉበት መሆኑን ገልጸዋል። የህዳሴ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ሱራፌል እሸቱ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው በ2013ቱ ምርጫ ወቅት የነበሩበትን ደካማ እና ጠንካራ ጎኖች ለይቶ የዘንድሮውን ምርጫ በከፍተኛ ዝግጅት ሲጠብቅ መቆየቱን ተናግረዋል። ፓርቲያቸው ምርጫው ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ሱራፌል፤ ከዚህ ጎን ለጎንም የምርጫ ማኒፌስቶውን እና ፕሮግራሞቹን በተሻለ መልኩ ማስተዋወቅ መቻሉን ገልጸዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከአየር ሰዓት አጠቃቀም ጀምሮ የመንገድ ላይ እና የአደባባይ ቅስቀሳዎችን በተሻለ ሁኔታ ማካሄድ የሚቻልበት አስቻይ ሁኔታ የተፈጠረበት መሆኑን ጠቅሰዋል። የነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ አባል እና የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ሰብሳቢ አቶ ኡመር አብዱራህማን፤ አጠቃላይ የዘንድሮው ምርጫ ሂደት የተሻለ እንቅስቃሴ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ የተፈጠረበት እና የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል። "የምርጫ ምህዳር አሳታፊነቱ በተለይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ነጻ የአየር ሰዓት አውጥቶ ሀሳባችንን በነጻነት ለህዝብ ተደራሽ እንድናደርግ ያመቻቸበት መንገድ እጅግ የሚበረታታ ነው" ብለዋል። የወለኔ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ፋይሰል አብዱልዓዚዝ እንዲሁ ዘንድሮ ከምርጫ ቦርድ ጀምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉበት ዓመት መሆኑን ጠቁመዋል። "ዘንድሮ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊ እና ግልጽ የሆነ ውድድር እንዲኖር ከማድረግ ረገድ እጅግ ጥሩ ሁኔታዎች የተፈጠሩበት የምርጫ ሂደት እየተመለከትን ነው" ሲሉም ተናግረዋል።
ፖለቲካ
ፓርቲው በሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚ አድርጓል
May 21, 2026 178
ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ባከናወናቸው ሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን የገንዳውኃ፣ ሰቆጣ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃንና ኮምበልቻ ከተሞች አስተያየታቸውን የሰጡ ሴቶችና ወጣቶች ገለጹ። በገንዳውኃ፣ ሰቆጣ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃንና ኮምቦልቻ ከተሞች “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!" በሚል መሪ ሐሳብ የቅስቀሳና ድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይ ከተሳተፉት መካከል ወይዘሮ የምስራች አበበ እንዳሉት፤ ፓርቲው ሴቶች ተደራጅተው መብትና ጥቅማቸውን እንዲያስጠብቁ አድርጓል ብለዋል። ሴቶችን ወደ አመራር በማምጣት፣ በተለያዩ ገቢ ማስገኛ ስራዎች እንዲሰማሩ በመደገፍና በልማት ስራዎች በማሳተፍ ኑሯቸውን እንዲቀይሩ ማድረጉን ገልጸዋል። ሌላዋ የድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊ ቤዛዊት አስናቀው ኢትዮጵያን በምግብ ራሷን በማስቻል ወደ ተሻለ እድገት ለማሻገር የተሰራው ስራ ፍሬ ማፍራቱን ጠቁመዋል። በብልጽግና ፓርቲ የገንዳውኃ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አስማረች ቆያቸው ፓርቲው የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በሰቆጣ ከተማ በተካሄደው ሰልፍ ላይ የተገኙት የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንታይቱ ካሴ እንደገለጹት ብልፅግና የህብረ ብሔራዊ አንድነትና የአብሮነት ተምሳሌት ነው ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ላቀች ሰማ እንዳሉት መንግስት ባለፉት ዓመታት ሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት ሰርቷል። በቀጣይም ሴቶችን በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች የላቀ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ እንደሚሰራ ገልጸዋል። ወይዘሮ ሰላም ተመስገን እና ወይዘሮ እመቤት አንዷለም እንዳሉት ፓርቲው የያዘውን ራእይ ለማሳካት የድርሻችን እንወጣለን ብለዋል። እንዲሁም በደብረ ብርሃን ከተማ የድጋፍ ሰልፍ ተሳታፊ የሆኑት ወይዘሮ አባይነሽ ሃይሉና ወይዘሮ ረድኤት በሻው እንደገለጹት ፓርቲው የጀመራቸውን የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደትን ከዳር ለማድረስ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወይዘሮ ዓለም መኩሪያ እንደገለጹት ፓርቲው ሴቶችና ወጣቶችን በማሳተፍ እየሰራ ይገኛል። በፓርቲው የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሙሉጌታ አቢ በከተማዋ በተካሄደው ሰልፍ ላይ እንደገለጹት ፓርቲው የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ መጪውን ትውልድ ለመገንባት አልሞ እየሰራ ይገኛል።
በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት በፈፀምነው ጥፋት በመጸጸት የልማት አርበኛ ለመሆን ተዘጋጅተናል-የቀድሞ ታጣቂዎች
May 21, 2026 208
ኮምቦልቻ፤ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት በፈፀምነው ጥፋት በመጸጸት የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር ለመሆን ተዘጋጅተናል ሲሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በአማራ ክልል ጫካ ገብተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል በኮምቦልቻ የተሃድሶ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት በፈፀምነው ጥፋት በመጸጸት የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር በመሆን ህዝብን ለመካስ ተዘጋጅተናል ብለዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አሸናፊ ደሳለኝ፥ ህዝቡ የሚፈልገው ሰላምና ልማት መሆኑን በተግባር አሳይቶናል ሲል ተናግሯል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት ህዝብን ለእንግልት፣ዘረፋና ችግር ዳርገናል ነው ያለው። በዚህም የመንግስትን ጥሪ ተቀብለን ሰላምን በማስከበርና ልማትን በመደገፍ ለመካስ ተዘጋጅተናል ብሏል። ታጣቂ አለፉ ንጉሴ እና ሃምሳ አለቃ ሞላ ጎሹ በበኩላቸው፥ ለአማራ ህዝብ እንታገላለን በሚል የተሳሳተ ፕሮፓጋንዳ በርካታ ወጣቶች መታለላቸውን አንስተዋል። የህዝብን ንብረት ከማውደም፣ከመዝረፍና እገታ ውጭ ሌላ አላማ አለመኖሩንም ተናግረዋል። በርካቶች በጥፋታቸው በመጸጸት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ስለመምጣታቸውም ጠቁመዋል። የአማራ ክልል ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አማካሪ ኮሎኔል ባምላኩ አባይ፤ በክልሉ በርካታ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ በመቀበል ስልጠና እየወሰዱ ወደ ማህበረሰቡ እየተቀላቀሉ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ለሰላም በሩ ክፍት በመሆኑ ጫካ ያሉ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርበዋል። በብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የስልጠና ዳይሬክተር ብርሃኑ ተስፋዬ፤ በተለያዩ አካባቢዎች የቀድሞ ታጣቂዎችን በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና እንዲወስዱና ህብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ እየተደረገ ነው ብለዋል። የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ ህዝቡን በልማት መካስ እንዳለባቸው በማሳሰብ በቀጣይም ተመሳሳይ ስራዎች የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል።
የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም ዘብ በመሆን የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል
May 21, 2026 233
ጎንደር ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ በመሆን የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ሲሉ የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ ገለጹ። የሠላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል የጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በመገኘት የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም(ዲዲአር) ፕሮግራምን አስጀምረዋል። ሚኒስትሩ በተሃድሶ ስልጠናው ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፤ መንግስት የሠላም ጥሪውን የተቀበሉ ታጣቂዎች የሠላም አምባሳደር በመሆን ህዝባቸውን እንዲክሱ የማቋቋም ስራ እያከናወነ ነው። የቀድሞ ታጣቂዎች ሠላምን አማራጭ በማድረግ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ በመሆን የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን ፤ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ህይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል። ብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽኑ በአማራ ክልል የሠላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም ወደ ማህበረሰቡ የመቀላቀል ስራ ማከናወኑን ተናግረዋል ። በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የአስተዳደር ጉዳዮች ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር)፤ በክልሉ የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም የሠላም ዘብ ሆነው እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ክልሉ አሁን ላይ ወደ አስተማማኝ ሠላም በመሸጋገሩ በርካታ የልማት ተግባራትን ማከናወን የተቻለበት ሁኔታ መፈጠሩን አመልክተዋል። የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ በሪሁን መንግስቴ፤ የሠላምን አማራጭ በመቀበል ወደ ክልሉ የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎች የሠላም አምባሳደር በመሆን እየሠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል ። የቀድሞ ታጣቂዎች የሠላም አማራጭ መከተላቸው ለክልሉ የሠላም ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የላቀ ነው ብለዋል። የሠላም ጥሪውን ተቀብለው ከገቡ የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል ባዬ ቀናው፤ በተከተልነው የተሳሳተ መንገድ ህዝብና መንግስትን በድለናል ብሏል። የሠላም ጥሪውን የተቀበልነው ለሠላም ካለን ቁርጠኛ አቋም በመሆኑ በልማት ስራዎች በመሳተፍ ህዝብና መንግስትን ለመካስ ዝግጁ ነን ሲል አክሏል። በተሀድሶ ስልጠና ማስጀመሪያ ስነ-ስርአቱ ላይ የፌዴራል፣ የክልልና የጎንደር ከተማ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያና አሜሪካን ታሪካዊ ግንኙነት ወደላቀ አጋርነት ማሸጋገር ያስቻለ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ሥራ ተሰርቷል
May 21, 2026 206
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና አሜሪካን ታሪካዊ ግንኙነት ወደላቀ አጋርነት ማሸጋገር ያስቻለ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ሥራ መሰራቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያን የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደላቀ ምዕራፍ ያሸጋገረ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፤ በሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ የተከናወኑ ዐበይት ክንውኖችን በማስመልከት ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ ባለፈው ሳምንት በሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ የኢትዮጵያን ትብብር፣ አጋርነትና የኢንቨስትመንት ምቹነት ያረጋገጡ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል። በሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የግንኙነት መድረኮቹም ጠንካራና ንቁ ዲፕሎማሲ ተሳትፎ ማድረግ ያስቻሉ እንደነበር አስታውሰዋል። ለአብነትም በኢትዮጵያና አሜሪካ መካከል የተደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች የሀገራቱን ከ120 ዓመታት በላይ የተሻገረ ታሪካዊና ጠንካራ ወዳጅነት ዘላቂና ተቋማዊ ማድረግ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። የሀገራቱ የሁለትዮሽ መዋቅራዊ የምክክር መድረክና ስምምነትም ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትን በማጠናከር ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በሁለትዮሽ ስምምነቱም የሀገራቱን ንግድና ኢንቨስትመንት፣ የፀጥታና መከላከያ ትብብር ወደላቀ ምዕራፍ በማሸጋገር የጋራ የኢኮኖሚ ብልፅግናን ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ እንደነበር አንስተዋል። በኢትዮጵያና አሜሪካ መንግስታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተደረገው የዲፕሎማሲ ምክክርም ታሪካዊ ወዳጅነትን ወደላቀ አጋርነት ለማሸጋገር ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን አብራርተዋል። በሁለትዮሽ መድረኮቹም የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገትና ብልፅግና ሞዴል እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ገለፃ መደረጉን አስረድተዋል። የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝትም የሀገራቱን ታሪካዊ ወዳጅነት ይበልጥ የሚያጎለብት የትብብር ስምምነቶች የተፈረመበት መሆኑን ገልጸዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 80ኛ ዓመትን በማስመልከትም የኢትዮጵያን መስራችነት፣ የሰላም ማስከበር ስኬታማ ተልዕኮና የጋራ ታሪክ የሚያሳይ ልዩ የቴምብር ስብስብ ማሳተሟን ጠቅሰዋል። ይህም ኢትዮጵያ ለባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነትና ታሪካዊ ትስስር የዘከረ መሆኑን ተናግረዋል። በሕንድ በተካሄደው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባም ኢትዮጵያ ሁሉንም ሀገራት በፍትሐዊነት የሚያገለግል ሥርዓት ሊዘረጋ እንደሚገባ ያላትን አቋም ማንፀባረቋን አስረድተዋል። ከብሪክስ ስብሰባ በተጨማሪ ከአባል ሀገራቱ ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችሉ ፍሬያማ ውይይቶች መካሄዳቸውን ተናግረዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም በደቡብ አፍሪካና ሳዑዲ አረቢያ ያሉ ዜጎችን ደኅንነት ማስጠበቅ የሚያስችሉ ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። የኢትዮጵያን ፍትሐዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ታሪካዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ለማስገንዘብ የሚደረጉ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
በክልሉ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን የሚያረጋግጡ የመደመር መንግስት ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች እየተተገበሩ ነው
May 21, 2026 229
ቴፒ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን የሚያረጋግጡ የመደመር መንግስት ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች በክልሉ እየተተገበሩ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። በክልሉ ቴፒ ከተማ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ የቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የመደመር መንግስት እኩል የምንደመጥበትን ምቹ አውድ ፈጥሯል ብለዋል። በዚህም ክልሉ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት አግኝቶ ያደሩ መሠረተ ልማቶችን ከማጠናቀቅ ባለፈ አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶችን አቅዶ በመተግበር ሕዝብን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ክልሉ ያለውን ጸጋ በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማምጣትና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ላይ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በፓርቲው መሪነት የተገኙ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ትሩፋቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም በጠቅላላ ምርጫው ህዝቡ ለፓርቲው ይሁንታ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው እንዳሉት፤ ፓርቲው የሕዝቡን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሰራ ነው። የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ በመመለስ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ህብረተሰቡን በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሕዝቡ በምርጫው ዕለት በነቂስ ወጥቶ ድምጹን ለፓርቲው በመስጠት ከጎኑ እንዲሆንም ጠይቀዋል። በክልሉ መልካም እሴቶችንና ወንድማማችነትን እያጎለበተ ያለው ብልጽግና ፓርቲ በዞኑ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ አድርጓል ያሉት ደግሞ የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ናቸው። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ፍትሐዊ የመልማት ዕድል ዞኑ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱን ገልጸው፣ የአካባቢውን እምቅ የተፈጥሮ ጸጋ ወደ ኢኮኖሚ ምንጭነት ለመቀየርም በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የመጀመሪያውን የምርጫ ካርዳችንን የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት እንጠቀምበታለን
May 21, 2026 178
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የመጀመሪያውን የምርጫ ካርዳቸውን የሀገርን ልማትና ዕድገት በማፋጠን የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት እንደሚጠቀሙበት የአዲስ አበባ ወጣቶች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጡበታል ተብሎ የሚጠበቀው ጠቅላላ ምርጫ ውስን ቀናት ቀርተውታል። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባም በተለያዩ ምዕራፎች በማካሄድና በማራዘም ከየካቲት 28 እስከ ሚያዚያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ ቆይቶ ተጠናቋል። በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ከ50 ሚሊየን 514 ሺ በላይ ዜጎች ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ መውሰድ ችለዋል። በጠቅላላ ምርጫው 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ታዛቢነት ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር ውስጥ ድርጅቶችም በተለያዩ አካባቢዎች ከ60 ሺህ 277 በላይ ወኪሎችን አሰማርተዋል። በመራጮች ትምህርት ላይ ዕውቅና የተሰጣቸው 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ለመራጩ ህዝብ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርትና ስልጠና እየሰጡ ይገኛል። የአዲስ አበባ ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ጠቅላላ ምርጫው ሕገ-መንግሥታዊ የመምረጥ መመረጥ መብት በአደባባይ የሚታይበት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ልምምድ መገለጫ ነው። ለዚህም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ማዕከላት በአካልና በዲጂታል አማራጭ የምርጫ ካርድ በማውጣት ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እንዳደረጉ ገልጸዋል። በሂደቱም የሀገርን ዘላቂ ልማትና ዕድገት በማፋጠን የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ እንደሚሰጡ አረጋግጠዋል። የ12ኛ ክፍል ተማሪዋ ወጣት መቅደላዊት ሁሴን፤ ምርጫ የሕገ-መንግሥታዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ልምምድ መገለጫ ነው ብላለች። በዚህም ለመጀመሪያ ጊዜ በወሰደችው የምርጫ ካርድ የተሻለ የፖሊሲ አማራጭ ላለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገልፃለች። ወጣት ዳዊት ወንደሰን በበኩሉ፤ በምርጫ ሂደት ዜጎች የሚኖራቸው የነቃ ተሳትፎ የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለመበየን የማይተካ ሚና እንዳለው ተናግሯል። በጠቅላላ ምርጫውም ሕገ-መንግሥታዊ መብቱን በመጠቀም ድምፅ እንደሚሰጥና ለምርጫው ስኬትም ገንቢ ሚና እንደሚወጣ አረጋግጧል። ወጣት ዳግማዊት ዳንኤልም፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንደወጣት የሚጠበቅባትን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብላለች። ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎች ድምፅ ሰጥቶ እንደማያውቅ ያስታወሰው ደግሞ ወጣት ምህረቱ በቀለ ነው። በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫም ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በመውሰድ ለሀገር ዕድገትና ወጣቶች ተጠቃሚነት ይበጃል የሚለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቱን አረጋግጧል።
የህዝብን የልማት ጥያቄ የሚመልስና ሀገርን የሚያሻግር ፖሊሲ ላለው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል
May 21, 2026 202
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦የህዝብን የልማት ጥያቄ የሚመልስ እና ሀገርን የሚያሻግር ፖሊሲ ላለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የሲዳማ ክልል ነዋሪዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ ተይዟል፡፡ ቦርዱ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረትም ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ50 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የምርጫ ካርድ የወሰዱ ሲሆን፣ ዜጎቹም በካርዳቸው ይሆነኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ ናቸው። ኢዜአ ያነጋገራቸው በሲዳማ ክልል የቡራ እና በንሳ ወረዳ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ በወሰዱት ካርድ ሀገር የሚያሻግር የፖሊሲ አማራጭ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ ነው፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡት የቡራ ወረዳ ነዋሪዎች መካከል አቶ አለማየሁ አርጋታ እና አቶ አዱኛ አማቼጅ እንደገለጹት፤ በጠቅላላ ምርጫው ድምጽ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የምርጫ ካርድ በወቅቱ ወስደዋል፡፡ በድምጽ መስጫው እለትም የተሻለ የፖለሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የፓርቲዎችን የቅስቀሳና የክርክር ሂደት እየተከታተሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የበንሳ ዳዬ ከተማ ነዋሪ ወጣት ዘላለም ዘነበ፣ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለሚያረጋግጥ ፓርቲ ድምጿን ለመስጠት ተዘጋጅታለች። ወጣቶች ለሀገር ሰላምና ዴሞክራሲ ግንባታ ያላቸውን ሚና በተግባር መወጣት እንዳለባቸው ገልጻ፣ በምርጫ ቀን ዴሞክራሲያዊ መብቷን ከመጠቀም ባለፈ ሰላማዊና ፍትሀዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሏን ለመወጣት መዘጋጀቷን ተናግራለች። ለወጣቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ይበልጥ ተግቶ የሚሰራ ፓርቲን ለመምረጥም ፓርቲዎች በተለያዩ መንገዶች የሚያደርጉትን ቅስቀሳ በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን ጠቁማለች። ምርጫው ከሂደቱ ጀምሮ ሰላማዊ፣ ፍትሀዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ለመወጣት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የበንሳ ወረዳ ነዋሪ አቶ ታደሰ ጎኖሶ ናቸው። ለሀገር ቀጣይነት ያለው እድገትና ለዜጎች ተጠቃሚነት ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ወሳኝ መሆኑን ያነሱት አቶ ታደሰ በዚህ ረገድም ተከታታይ ትምህርትና ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
የምርጫ ሂደቱ ምቹ የፖለቲካ ምህዳርና አስቻይ ሁኔታዎች የተፈጠሩበት ነው- የፖለቲካ ፓርቲዎች
May 21, 2026 261
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ምቹ የፖለቲካ ምህዳርና አስቻይ ሁኔታዎች የተፈጠሩበት መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የዘንድሮው የምርጫ ሂደትና አጠቃላይ ቅንጅት ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ያስቻለ ስለመሆኑም የፓርቲ አመራሮቹ ተናግረዋል። አጠቃላይ የእስካሁኑን የምርጫ ሂደት አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ምቹ የፖለቲካ ምህዳርና አስቻይ ሁኔታዎች የተፈጠሩበት መሆኑን ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሃፊ እና የኢዜማ ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ታሪኩ ድንበሩ፤ በጋራ ምክር ቤቱም ሆነ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ለምርጫው ዴሞክራሲያዊነት እና ሰላማዊነት በትብብር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። በተለይም የጋራ ምክር ቤቱ የምርጫ እቅድ አዘጋጅቶና ኮሚቴ አዋቅሮ ወደ ስራ መግባቱን የገለጹት አቶ ታሪኩ፤ በ21 የክልሉ ዞኖች እና በ213 ወረዳዎች ምክር ቤት ተቋቁሞ የተሻለ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። በምክር ቤቱ ስር የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተሻለ መልኩ ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን፣ በሂደቱ ያጋጠሙ ችግሮችም በፍጥነት እየተፈቱ መሆኑን አረጋግጠዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በቀደሙት ምርጫዎች ወቅት እንደ ስጋት የሚታዩ ችግሮች የተቀረፉበት እና ምርጫው ሰላማዊ፣ ተአማኒ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት በጋራ እየሰሩ ያሉበት መሆኑን ገልጸዋል። የህዳሴ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ሱራፌል እሸቱ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው በ2013ቱ ምርጫ ወቅት የነበሩበትን ደካማ እና ጠንካራ ጎኖች ለይቶ የዘንድሮውን ምርጫ በከፍተኛ ዝግጅት ሲጠብቅ መቆየቱን ተናግረዋል። ፓርቲያቸው ምርጫው ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ሱራፌል፤ ከዚህ ጎን ለጎንም የምርጫ ማኒፌስቶውን እና ፕሮግራሞቹን በተሻለ መልኩ ማስተዋወቅ መቻሉን ገልጸዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከአየር ሰዓት አጠቃቀም ጀምሮ የመንገድ ላይ እና የአደባባይ ቅስቀሳዎችን በተሻለ ሁኔታ ማካሄድ የሚቻልበት አስቻይ ሁኔታ የተፈጠረበት መሆኑን ጠቅሰዋል። የነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ አባል እና የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ሰብሳቢ አቶ ኡመር አብዱራህማን፤ አጠቃላይ የዘንድሮው ምርጫ ሂደት የተሻለ እንቅስቃሴ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ የተፈጠረበት እና የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል። "የምርጫ ምህዳር አሳታፊነቱ በተለይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ነጻ የአየር ሰዓት አውጥቶ ሀሳባችንን በነጻነት ለህዝብ ተደራሽ እንድናደርግ ያመቻቸበት መንገድ እጅግ የሚበረታታ ነው" ብለዋል። የወለኔ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ፋይሰል አብዱልዓዚዝ እንዲሁ ዘንድሮ ከምርጫ ቦርድ ጀምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉበት ዓመት መሆኑን ጠቁመዋል። "ዘንድሮ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊ እና ግልጽ የሆነ ውድድር እንዲኖር ከማድረግ ረገድ እጅግ ጥሩ ሁኔታዎች የተፈጠሩበት የምርጫ ሂደት እየተመለከትን ነው" ሲሉም ተናግረዋል።
ማህበራዊ
በክልሉ ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ይበልጥ ለማስፋፋት የተቀናጁ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው
May 21, 2026 128
ጅግጅጋ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል ጥራት ያለውና ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ይበልጥ ለማሳደግ ዘላቂ ስራዎች በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢብራሂም ኡስማን ገለጹ። የሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ 1ኛውን ዓመታዊ የጤና አገልግሎት ጥራት እና ኢኖቬሽን ጉባኤ በጅግጅጋ ከተማ እያካሄደ ነው። የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢብራሂም ኡስማን በጉባኤው ባደረጉት ንግግር መንግስት ቀልጣፋ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ ከፍተኛ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ተቋማትን ተደራሽነት ለማስፋፋት፣ የሠለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራትና የሕክምና ግብዓቶችን ለማሟላት ሰፊ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በዚህም የጤና አገልግሎቱን በዲጂታል ሥርዓት በመደገፍ፥ ለኅብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ ምቹና ተደራሽ በሆነ መንገድ ለመስጠት በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ እንደገለጹት ከለውጡ በኋላ መንግስት ለክልሉ የሠጠው ትኩረት በርካታ ስኬቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል። የጤናውን ዘርፍ በግብዓትና በሰለጠነ የሰው ሀይል በማሟላት ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት በተለይም በአርብቶ አደሩ ማኅበረሰብ ዘንድ ተደራሽ እንዲሆን ከፍተኛ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። የሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሙሴ አህመድ በበኩላቸው፤ የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ በማድረግ ተቋማቱ ለኅብረተሰቡ ምቹና ጥራት ያለው እንክብካቤ መስጠት እንዲችሉ ሰፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተለይም በእናቶችና ሕፃናት ጤና አጠባበቅ በኩል ከፍተኛ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ከለውጡ ወዲህ በክልሉ ስድስት የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከላት መገንባታቸውንና ከእነዚህም መካከል ወደ ሥራ የገቡ መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ለአብነትም በ240 ሚሊየን ብር ወጪ በካራማራ አጠቃላይ ሆስፒታል የተገነባው የፌስቱላ ማዕከልና የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከል ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ተናግረዋል። የአሁኑ ጉባኤም ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ሊያሳድጉ የሚችሉ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎች፣ የመድኃኒትና የሕክምና ግበዓቶች አቅርቦቶች፣ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶች እንዲሁም የልምድ ልውውጦች የሚቀርቡበት መሆኑን ኃላፊው ገልጸዋል። ለሁለት ቀናት በተሰናዳው ጉባዔ የፌዴራልና የክልል የዘርፉ አመራሮች እና የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች ተወካዮች እየተሳተፉ ናቸው።
ኢትዮጵያ የአደጋ ሥጋትን በመቀነስ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማጠናከር የሚያስችል ውጤት እያስመዘገበች ነው
May 21, 2026 127
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአደጋ ሥጋትን በራስ አቅም ምላሽ በመስጠት የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማጠናከር የሚያስችል ውጤት እያስመዘገበች መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) ገለጹ። የአፍሪካ መሪዎች በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸደቀውንና እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር ከ2015 ጀምሮ ለ15 ዓመታት የሚቆየውን የሰንዳይ ማዕቀፍ ተከትሎ አባል ሀገራት በየሁለት ዓመቱ የአደጋ ሥጋት ቅነሳ ግምገማ እንዲካሄድ ውሳኔ አሳልፈዋል። በዛሬው ዕለትም 4ኛው ዙር የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት የአደጋ ሥጋት ቅነሳ ግምገማ በሕብረቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል። የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) በዚህ ወቅት፤ የአፍሪካ ሀገራት አደጋዎች እያስተናገዱ ቢሆንም የዓለም አቀፍ አጋርነት እያሽቆለቆለ ነው ብለዋል። የአህጉሪቱን የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ተጋላጭነት ለመቀነስም በአባል ሀገራት መካከል የአደጋ ሥጋት ቅነሳ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችል ትብብር መጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነት ፍኖተ ካርታና ፓኬጅ በመቅረፅ ድጋፍ የሚስፈልጋቸውን የመለየትና የመደገፍ ሥራ እየሰራች መሆኑን ተናግረዋል። የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ተጋላጭነትን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት የእሳትና ቅፅበታዊ አደጋዎች ደንብን በማፅደቅ ጭምር እየተሰራበት መሆኑን አንስተዋል። የስትራቴጂክ መጠባበቂያ ክምችት አቅምን በማጎልበት ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ምላሽ መስጠት የሚያስችል አስተማማኝ አቅም እየተፈጠረ መምጣቱን ጠቅሰዋል። የተረጂነት ባህልና አስተሳሰብን ለመቀየርም በቤተሰብና በማህበረሰብ ደረጃ የአምራችነትን ባህል ማጎልበት የሚያስችል ግንዛቤ እያደገ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም በአፍሪካ የአደጋ ሥጋት ተፅዕኖ ቅነሳ ማዕቀፍ ስር በፖሊሲና ስትራቴጂክ አሰራር የሚመራ ተምሳሌታዊ ውጤት እየተገኘ መሆኑን አስረድተዋል። በአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዘላቂ አካባቢና ብሉ ኢኮኖሚ ዳይሬክተር ሀርሰን ንያምቤ በበኩላቸው፤ በአፍሪካ የአደጋ ሥጋት ቅነሳ ግምገማ የሞት መጠን እየቀነሰ መጥቷል ብለዋል። የአህጉሪቱን የአደጋ ሥጋት በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠትም አሕጉራዊ የአደጋ ምላሽ ፈንድ በማቋቋም በትብብር መስራት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። የዓለምአቀፍ አጋሮች የአፍሪካን የአደጋ ሥጋት የመረዳት ፍላጎት እየቀነሰ በመምጣቱ ትብብርን የሚያጠናክር ፖሊሲና ተቋማዊ አቅም በመገንባት በጋራ መስራት ይገባል ብለዋል።
ኢንስቲትዩቱ አዳዲስ ተመራማሪዎችን እና የጤና ባለሙያዎችን በማሰልጠን ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል
May 21, 2026 143
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ አርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ምርመራን ከማሻሻል ባለፈ አዳዲስ ተመራማሪዎችን እና የጤና ባለሙያዎችን በማሰልጠን ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ገለጹ። ኢንስቲትዩቱ በሕክምናው ዘርፍ በወባ በሽታ ላይ የላቀ የምርምር ሥራ ያከናወኑ ለሦስት ወጣት ተመራማሪዎች የ23ኛውን «ቶሬ ጎዳል» የሳይንስ እውቅና ሽልማት ዛሬ ሰጥቷል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ በሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ዓመታት እንደ ቲቢ፣ ወባ፣ ኤች.አይ.ቪ፣ ሄፓታይተስ፣ ኮሌራ፣ ኒሞኒያ እና ማጅራት ገትር በካንሰር እና በተለያዩ በሽታዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሰፊ ምርምር ሲያደርግ ቆይቷል። እንዲሁም በጤና ፈጠራዎች፣ በክሊኒካዊ ሙከራዎች፣ በክትባት ምርምር፣ በባህላዊ ሕክምና እና በፋርማሲዩቲካል ኢንዱስትሪ ልማት ዙሪያ ግንባር ቀደም ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። ኢንስቲትዩቱ የበሽታዎችን መከላከል፣ መቆጣጠር እና ምርመራን ከማሻሻል ባለፈ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር አዳዲስ ተመራማሪዎችን እና የጤና ባለሙያዎችን በማሰልጠን ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ጨምረው አስታውቀዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር) የተመረቀው አዲሱ የምርምር ማዕከል እና ተያያዥ ፋሲሊቲዎች ሀገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ፋይዳ ያላቸው ትልቅ ሀብቶች መሆናቸውን አንስተው ለዚህ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ በሕክምናው ዘርፍ ከፍተኛና ውጤታማ የምርምር ሥራዎችን በማከናወን የ"ቶሬ ጎዳል" ሽልማትን ያገኙት ተሸላሚዎች በሙሉ የተሰማቸውን ኩራት ገልጸዋል፡፡ የዕለቱ ሽልማትም ለሀገር የሚጠቅም ምርምር የሚያደርጉ ወጣት ተመራማሪዎች እንዲወጡ ትልቅ አቅም እንደሚሆንም ጨምረው አስታውቀዋል። ሽልማቱን የተቀበሉት ወጣት ተመራማሪዎች በበኩላቸው የተበረከተላቸው እውቅና ለቀጣይ የምርምር ሥራዎቻቸው ትልቅ ጉልበትና መነሳሳት እንደሚሆናቸው ገልጸው፤ በቀጣይም በሕክምናው ዘርፍ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል። ዘንድሮ ለ23ኛ ጊዜ በተካሄደው በዚህ የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ የመንግሥት ተቋማት፣ ኤምባሲዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በኖርዌያዊው የሕክምና ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ቶሬ ጎዳል የተሰየመው ይህ ሽልማት በኢትዮጵያ በጤና ምርምር ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ወጣት ተመራማሪዎች ይበረከታል፡፡
በክልሉ የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋንን ለማሳደግ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ስራዎች ላይ፣ የአጋር አካላት ሚና የጎላ ነው
May 21, 2026 172
አሶሳ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋንን ለማሳደግ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ስራዎች ላይ፣ የአጋር አካላት ሚና የጎላ መሆኑን የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ መንጌ ወረዳ ፋሮ ፋውንደሽን የተሰኘ ድርጅት ያስገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። በዕለቱ የተገኙት የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ሀጂራ ኢብራሂም እንደተናገሩት፤ የህብረተሰቡን የንፁህ መጠጥ ውሃ ጥያቄ ለመመለስ በመንግስት በኩል እየተከናወኑ ከሚገኙ ስራዎች በተጨማሪ የአጋር ድርጅቶች ዕገዛ ከፍተኛ ነው። በመንጌ ወረዳ የተገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትም የህብረተሰቡን የንፁህ መጠጥ ውሃ ጥያቄ የመለሰ እና ህብረተሰቡ በንፁህ መጠጥ ውሃ ፍለጋ ሲደርስበት የነበረውን ድካም እና እንግልት ያስቀረ ነው ብለዋል። ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ በፀሐይ ሃይል የሚሰራ በመሆኑ ከአከባቢው የአየር ሁኔታ ጋር የሚጣጣም እና የረጂም ጊዜ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። የፋሮ ፋውንደሽን ከፍተኛ የኮንስትራክሽን ባለሙያ ኢንጂነር ሀብታሙ ሀይሌ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ በክልሉ በትምህርት፣ በጤናና ንፁህ የመጠጥ ውሃ ግንባታዎችን በማከናወን የህብረተሰቡን ችግር በማቃለል ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በመንጌ ወረዳ ሁለት ቀበሌዎች ላይ የተገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትም 12 የውሃ ቦኖዎችን ያካተተ ሲሆን ከ11 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎት አንደሚሰጥ ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ በ10 ወራት ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀ መሆኑን ገልፀው ፕሮጀክቱ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበትም አስታውቀዋል። ፋሮ ፋውንዴሽን በወረዳው የተለያዩ የልማት ስራዎችን በማከናወን የህብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች በመመለስ አጋርነቱን እያሳዬ ነው ያሉት ደግሞ የመንጌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አጠይብ ናቸው። ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ የወረዳው ነዋሪዎች አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርጉም ዋና አስተዳዳሪው አሳስበዋል።
ኢኮኖሚ
በክልሉ ለአምራች ኢንዱስትሪው በተሰጠ ትኩረት በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር እያደገ መጥቷል - አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
May 21, 2026 110
ሀዋሳ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ለአምራች ኢንዱስትሪው በተሰጠ ትኩረት በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር እያደገ መምጣቱን የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ። በሀዋሳ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ዛሬ ተመርቋል። የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ እንዳሉት እንደ ሀገር በተፈጠረው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ በአምራች ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት ታይቷል። ለአምራች ኢንዱስትሪው በተሰጠው ልዩ ትኩረትም በክልሉ በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር እያደገ መምጣቱ ተናግረዋል። አምራች ዘርፉ ከፍተኛ የሰው ሃይል የሚፈልግ በመሆኑ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል። ከአነስተኛ ወደ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ማደግ እንደሚቻል አበባ ጨርቃ ጨርቅና ቆዳ ስፌት አክሲዮን ማህበር ያስገነባው የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ አንድ ማሳያ ነው ብለዋል። የክልሉ አንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበሩ በበኩላቸው መንግስት አምራች ኢንዱስትሪውን በማበረታታት በርካቶችን ወደ ሥራ እንዲገቡ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ በክልሉ የተለያዩ ባለሀብቶች በአምራች ኢንዱስትሪው መስክ እንዲሰማሩ ለማበረታታትም በዘርፉ ለሚሰማሩ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው ምቹ ቦታዎችን ማዘጋጀቱንም ተናግረዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ አገና ኔቶ እንዳሉት በከተማዋ ከ1 ሺህ በላይ አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ይገኛሉ። ኢንዱስትሪዎቹ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡትን በማምረት በኢኮኖሚው ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆናቸውንም አስታውቀዋል። የአበባ ጨርቃ ጨርቅና ቆዳ ስፌት አክሲዮን ማህበር ሥራ አስኪያጅ ወሌ አበጋዝ (ዶ/ር) በበኩላቸው ለፋብሪካው ግንባታ ከ582 ሚሊዮን በር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት ፋብሪካው ለ153 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል መፍጠሩን ገልጸው፣ በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባ ለ310 ሰዎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በመታገዝ ወደ ኤክስፖርት ምርት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፣ ጥራት ያለው ምርት ለማምረትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በፋብሪካው የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል ወጣት ኤደን ዘርፉ እንዳለችው በፋሽን ዲዛይን ትምህርት መስክ ተመርቃ በፋብሪካው መቀጠሯን ተናግራለች።
በክልሉ በግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ወጣቶችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ላይ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ
May 21, 2026 64
ሀዋሳ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ወጣቶችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ላይ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለፀ፡፡ በሲዳማ ክልል የእርሻውን ዘርፍ ለማዘመንና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት በማለም የእርሻ ትራክተሮችን በዘርፉ ለተደራጁ ወጣቶች የማስረከብ መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡ በዚህ ወቅት የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ እንዳሉት፤ በክልሉ እየተከናወኑ ባሉ የግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ሥራዎች ወጣቶችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ ይገኛል። የግብርና እና ገጠር ትራንፎርሜሽንን ለማረጋገጥ ግቦች ተጥለው ማሳካት የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የምግብና ሥነ ምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ፣ ለገበያ የማምረት፣ ኤክስፖርትን የማሳደግና ገቢ ምርትን የመተካት እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ የግብርና ምርቶችን በስፋት የማምረት ግቦች እንዳሉ ጠቅሰዋል፡፡ በግብርና ዘርፍ ለተደራጁ ወጣቶች የእርሻ ትራክተሮች ርክክብ መከናወኑን ገልፀው በዚህም በአጠቃላይ 148 ወጣቶች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አስረድተዋል፡፡ የአካታችና ዘላቂ የግብርና እሴት ሰንሰለት ልማት ፕሮጀክት ብሔራዊ አስተባባሪ ሰለሞን ዳኜ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በገጠር በተለይ ወጣቶችና ሴቶችን አደራጅቶ ተሳታፊ በማድረግ የገጠሩን ኢኮኖሚ የማሳደግ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በመሆኑም ምርትና ምርታማነትን በማስፋትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት በኩል ፕሮጀክቱ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ትራክተሮቹን ከተረከቡ ማህበራት መካከል የቦና ወረዳ ወጣት ንግስት አምሳለ ማህበራቸው በቆሎ፣ ስንዴ እንዲሁም አቮካዶ፣ ማንጎና ሌሎች የተለያዩ ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ፍራፍሬዎችን እንደሚያመርት ገልፃለች፡፡ ከዚህ ቀደም የግብርና ሥራውን ባህላዊ በሆነ መንገድ ስለሚያከናውኑ ውጤታማነታቸው እምብዛም እንደነበር ገልፃ አሁን ላይ ሰፊ መሬትን በትራክተር በተሻለ ሁኔታ በማረስ ተጠቃሚ የሚያደርጋቸውን ዕድል እንዳገኙ ተናግራለች፡፡ የዳራ ወረዳ ወጣት አዲሱ ሌላሞ በበኩሉ ማህበራቸውም ሆነ በአካባቢያቸው ያሉ አርሶ አደሮች በበሬ አልያም በጉልበት የእርሻ ሥራቸውን እንደሚያከናውኑ ተናግሯል፡፡ ትራክተሮቹን የራሳቸውን እንዲሁም በአካባቢያቸው ያሉ አርሶ አደሮችን ማሳ ለማረስ እንደሚጠቀሙባቸው ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልፅግና በልጆቿ ጥረት ዕውን ማድረግ እንደሚቻል የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ ህያው ምስክር ነው
May 21, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልፅግና በልጆቿ ጥረት ዕውን ማድረግ እንደሚቻል የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ ህያው ምስክር መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኩን የጎበኙ የመዲናዋ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ግንቦት 8 ቀን 2018 የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን መርቀው ሥራ ማስጀመራቸው ይታወቃል። ከአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎችም የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የልማት ውጤትና የአምራቾችን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት የተጠሪ ተቋማት ዘርፍ ኃላፊ ዳዲ ወዳጆ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኢንዱስትሪ ክላስተር መሆኑን ገልጸዋል። የኢንዱስትሪ ፓርኩም የአምራቾችን ዓለም አቀፍ የተወዳዳሪነት አቅም በመገንባት ሀገራዊ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት ገንቢ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ለዚህም ፓርኩ የአዲስ አበባና የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥን የኢንዱስትሪ ምርታማነትን ምኅዳር እንደፈጠረ አንስተዋል። አዲስ አበባ በሁሉም ዘርፍ ስኬታማና ውጤታማ የልማት ሥራዎችን ዕውን የምታደርግ ከተማ መሆኗን የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ እንደሚያሳይ አስረድተዋል። የኢንዱስትሪ ፓርኩም ለመካከለኛና ከፍተኛ አምራቾች ምቹ የሥራ ከባቢ በመፍጠር በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በተኪና ወጪ ንግድ የምርት አቅም መገንባት የሚያስችላቸው መሆኑን አብራርተዋል። ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የመጣው አብዱራሂም አስገዶም፤ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ኢትዮጵያዊያን መስራትና ለውጥን ማምጣት እንደሚችሉ የሚያሳይ አስደናቂ የልማት ውጤት ነው ብሏል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልፅግና በልጆቿ ጥረት ዕውን ማድረግ እንደሚቻል የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ ህያው ምስክር መሆኑን ተናግሯል። ሌላኛው ከለሚኩራ የመጣው አስቻለው ሙሉጌታ በበኩሉ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ አምራቾች የሚገጥማቸውን የመስሪያ ቦታ ችግር የሚቀርፍ የልማት አቅም መሆኑን ገልጿል። የጉለሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪዋ የጉብኝቱ ተሳታፊ ፍጹም አምሳሉ፤ የኢንዱስትሪ ፓርኩ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት አቅም የሚሆን የማምረቻ ከባቢ መሆኑን ተናግራለች። የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ በርካታ የመዲናዋ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ አስደናቂ ፕሮጀክት ነው ያለው ደግሞ ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ የመጣው ዮኃንስ ሰለሞን ነው። ፓርኩም የተኪ ምርታማነትን በማሳደግ ለሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ገበያ መቅረብ የሚችሉ የኢንዱስትሪ ምርቶችን የማምረት አቅም እንደሚያጎለብት ማየቱን ተናግሯል።
መንግስት ለህዝብ የገባውን ቃል ይፈፅማል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
May 21, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት ለህዝብ የማይሰራውን ቃል አይገባም፤ ለህዝብ የገባውን ቃል ይፈፅማል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬም የኑሮ ውድነትን ለማቃለል፣ ምርት በብዛት ማቅረቢያ እና የግብይት ማዕከላት የማስፋት ስራችን አካል የሆነው 7ኛውን የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከልን ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል ብለዋል። ማዕከሉ የኑሮ ውድነትን የሚያቃልሉ ዘመናዊ፣ ማሞቂያ እና ማቀዝቀዣ ያላቸው 221 መጋዘኞች፥ የችርቻሮ ሱቆች፥ ሱፐር ማርኬቶች፣ ወፍጮ ቤቶች፣ በአንድ ጊዜ 250 ተሽከርካሪዎችን ማቆም የሚችል ፓርኪንግ፣ ለለሚ ኩራ፣ ለቦሌ እና የካ ክፍለ ከተሞች ነዋሪዎች በአማካይ ቦታ እና ሰሚት ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ምቹ የሆነ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ነው ብለዋል። በገበያ ማዕከሉ ማህበረሰቡ ለዕለት ፍጆታ የሚጠቀምባቸውን የሰብል ምርቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬዎች፣ የበርበሬ ፣የቅመማቅመም ምርቶች እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን የአንድ ማዕከል የግብይት ስርዓትን እውን ማድረግ መቻሉን ነው ከንቲባዋ የገለጹት። በማዕከሉ የሚቀርቡ ምርቶች ከ15 እስከ 20 በመቶ የዋጋ ቅናሽ የሚሸጥበት፥ ዋጋ የሚያንረውን ህገ-ወጥ የደላላ ሰንሰለት በመበጣጠስ ከአምራቹ ያልተቋረጠ ምርት የሚቀርብበትና የከተማዋ ነዋሪዎችን የኑሮ ጫና እንደሚያቃልል አመልክተዋል። በገበያ ማዕከሉ ከተለያየ ቦታ በኮሪደር ልማት የተነሱ ነዋሪዎችን ጨምሮ ማዕከሉ ያረፈበትን 3 ነጥብ 2 ሄክታር መሬት ለልማት የለቀቁ አርሶ አደሮችም ሱቅ እንዲያገኙ መደረጉንና በዚህም ለነዋሪዎች ሰፊ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር እንዲሳካ ጥረት ላደረጉ የዲዛይንና የኮንስትሪክሽን ስራዎች ቢሮ አመራርና ሰራተኞች፣ የንግድ ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች፣ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አመራሮች፣ ቦታው ለልማት እንዲውል ለሰጣችሁ አርሶ አደሮች በራሴና እና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመሰግናለሁ ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በማረጋገጥ የሳይበር ደኅንነት ስጋትን የሚቀለብስ የሰው ሃይል ማፍራት እየተቻለ ነው
May 21, 2026 100
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በማረጋገጥ የሳይበር ደኅንነት ስጋትን የሚቀለብስ የሰው ሃይል ማፍራት እየተቻለ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ገለጸ። አስተዳደሩ በዘንድሮው ክረምት ለ5ኛ ጊዜ የሚያካሂደውን የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ (Cyber Talent Summer Camp) ዝግጅት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። የአስተዳደሩ የሳይበር ልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር ቢሻው በየነ በመግለጫቸው፤ መርሃ ግብሩ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች በማሰልጠን የሳይበር ደኅንነትና የቴክኖሎጂ ሙያተኞችን ለማፍራት ያለመ ነው ብለዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያን የሳይበር ደኅንነትና ሉዓላዊነት የማስጠበቅ አቅምን የበለጠ ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ ኢትዮጵያ በዘርፉ ሀገራቸውን ከሳይበር ጥቃት የሚከላከልና ብቁ የሳይበር ሠራዊት ማፍራት መሆኑን አብራርተዋል። እንደ እስራኤል፣ እንግሊዝ እና አሜሪካ ያሉ ሀገራት ተሞክሮ መርሀግብሩ ታዳጊዎችን ለማፍራት ያለውን ወሳኝነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። ይህ ካምፕ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግና የኢትዮጵያን ዲጂታል ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። የዘንድሮው የስልጠና ካምፕ በክልል ደረጃ በስድስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲካሄድ የተወሰነ ሲሆን ይህም ታዳጊዎች በቅርበት ስልጠናውን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል። በእስካሁኑ ሂደትም ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ከ4 ሺህ በላይ ታዳጊዎችና ወጣቶች መመዝገባቸውን ገልፀዋል። ምዝገባውም ግንቦት 17/2018 ዓ.ም የሚጠናቀቅ በመሆኑ በሳይበር ደህንነትና ቴክኖሎጂ ልዩ ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎችና ወጣቶች በኦንላይን እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
የምርት ጥራት ደረጃ ማረጋገጫ መተግበሪያው የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው
May 21, 2026 103
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ የምርት ጥራት ደረጃ ማረጋገጫ መተግበሪያው የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት አፈጻጸም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በዛሬው ዕለት የምርት ጥራት ደረጃን በኦንላይን ማረጋገጥ የሚያስችል መተግበሪያ አስመርቆ ወደ ስራ አስገብቷል። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሠረት በቀለ (ዶ/ር) ተገኝተዋል፡፡ ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርሙ በንግድ ስርዓቱ ላይ ትልቅ እመርታ እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከ46 በላይ አገልግሎቶች በኦንላይን እየተሰጡ እንደሚገኙ ጠቅሰው፥ ይህም የንግድ ሥርዓቱን በማዘመን የምርት ጥራት አፈፃጸም ላይ የላቀ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት አስር ወራት ብቻ ከወጪ ንግድ ከ8 ነጥብ 7 ቢሊየን በላይ የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱንም ነው የተናገሩት፡፡ ዛሬ የተመረቀው የኦንላይን መተግበሪያ አገልግሎቶችንና የምርት ጥራትን በላቀ አፈፃጸም መምራት የሚያስችል መሆኑንና የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት አፈፃጸም ውጤታማነት ለማላቅ አይነተኛ ሚና ያበረክታል ብለዋል። የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሠረት በቀለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ተስፋ ሰጭ የለውጥ ጉዞ እያስመዘገበች ትገኛለች ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ የለውጥ ጉዞውን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሕግና ተቋማዊ ማሻሻያዎችን እንዳደረገ በመግለጽ፡፡ የዚህ ጥረት አካል የሆነው የኦንላይን የምርት ጥራት ማረጋገጫ መተግበሪያ የኢትዮጵያ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ በዋጋና በጥራት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑንም አክለዋል፡፡ መተግበሪያው የኢንስቲትዩቱን የማስፈጸም አቅም ሀገሪቱ ከደረሰችበት የዕድገት ደረጃ ጋር እንዲጣጣም አጋዥ ስለመሆኑም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በምርት ጥራት ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ እንደሚሆኑ የተናገሩት ደግሞ የአፍሪካ የደረጃዎች ተቋማት የማዕከላዊ ኮሚቴ ጸሐፊ ሬዩበን ጊሶር ናቸው፡፡ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወናቸውን አጠቃላይ ተቋማዊ የሪፎርም ስራዎችን አስመርቋል።
የሕክምና ሙከራዎች ፈቃድ የመስጠትና የቁጥጥር ሥርዓቱን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚያስችል ሥርዓት ተዘርግቷል
May 21, 2026 139
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦አዳዲስ የሕክምና ሙከራዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ ፈቃድ የመስጠትና የቁጥጥር ሥርዓቱን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋቱን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የሕክምና ሙከራ የቁጥጥር አሠራር የምክክር መድረክ ላይ አዲስ የተገነባውን የሕክምና ሙከራ የኦንላይን ማመልከቻ ሥርዓት (Online Application System) ማስጀምሪያ መርሃ ግብር አካሄዷል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬሕይወት አበበ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፤ ደህንነታቸውና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ አዳዲስና በሙከራ ላይ የሚገኙ የሕክምና መሣሪያዎች፣ መድኃኒቶችና ሌሎች ግብዓቶች በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገቡ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። አዳዲስ የሕክምና ሙከራዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ ፈቃድ የመስጠትና የቁጥጥር ሥርዓቱን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋቱን ተናግረው፤ ይህም ለሕብረተሰቡ ጤናና ደህንነት መጠበቅ ጉልህ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው የኦንላይን የቁጥጥር ስርዓትም የሕክምና ሙከራዎች ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር አገልግሎትን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ የሚያደርግ መሆኑን አብራርተዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለኢትዮጵያ የሚቀርቡ የሕክምና ሙከራ ፈቃድ አገልግሎት ጥያቄዎች እየጨመሩ መሆኑን ጠቅሰው፤ መተግበሪያው ሀገሪቱ የምታደርጋቸውን ዓለም አቀፍ ትብብሮች ይበልጥ ያጠናክራል ብለዋል። የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ በበኩላቸው፤ አዳዲስ የሕክምና ሙከራዎች የሕብረተሰቡን ጤናና ደህንነት ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። የሕክምና ሙከራዎች ፈቃድና ቁጥጥርን በዓለም አቀፍ መስፈርቶች መሠረት ዲጂታላይዝ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። ለአብነትም የማርበርግ ቫይረስ ሕክምናን ወደ ተግባር ለማስገባት ፈጣን ምላሽና ቀልጣፋ አገልግሎት በመሰጠቱ የቫይረሱን ስርጭት መግታት መቻሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በሕክምና ሙከራ አገልግሎት ዘርፍ ከአፍሪካ ተመራጭ ሀገር ለመሆን በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።
በቅመማ ቅመም ምርት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር እየተስፋፋ ነው
May 20, 2026 511
ቴፒ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ በቅመማ ቅመም ምርት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ዝግጅት ሂደትን የማስፋፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል አስታወቀ። ማዕከሉ የእርድ ምርትን ለገበያ ለማቅረብ የሚደረገውን ልማዳዊ አሰራር የሚያስቀር አዲስ ቴክኖሎጂ ለአርሶ አደሮች አስተዋውቋል። የእርድ ምርትን በባህላዊ መንገድ ለማዘጋጀት የሚደረገው የመቀቀል ሂደት ከፍተኛ የእንጨት፣ የውሃ፣ የጊዜና የጉልበት ብክነትን የሚያስከትል እንደሆነ ተገልጿል። የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ደረጀ ቱሉ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ባደረገው የምርምር ሥራ ያስተዋወቀው አዲስ ቴክኖሎጂ የምርቱን ጥራት በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያስጠብቅ ነው። በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ምርት ለማቅረብ ጥራት ትልቅ ትርጉም እንዳለው የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ አዲሱ የእርድ ማዘጋጃ ማሽን ጊዜና ጉልበትን በእጅጉ የሚቆጥብ መሆኑን አስረድተዋል። የቅመማ ቅመም ምርቶችን በብሔራዊ ደረጃ የሚያስተባብረው ይህ ማዕከል፤ የእርድ ሰብልን በክልሉ በስፋት ማስተዋወቁን ገልጾ፣ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ የማሰራጨት ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በማዕከሉ የቅመማ ቅመም ምርት ብሔራዊ አስተባባሪና ተመራማሪ የሆኑት አቡኪያ ጌቱ በበኩላቸው፤ አዲሱ የእርድ መክተፊያ ማሽን ከዚህ ቀደም ሦስት ሳምንታት ይፈጅ የነበረውን የምርት ዝግጅት ጊዜ ወደ 5 ቀናት ዝቅ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በላብራቶሪ በተደረገ ፍተሻ በማሽኑ የተዘጋጀው ምርት የተሻለ የጥራት ደረጃ መያዙ መረጋገጡንና ይህም ለሀገር ውስጥና ለዓለም ገበያ ከባዕድ ነገሮች የጸዳ ምርት ለማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል። የሸካ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ አዳምሰገድ ኃይለኢየሱስ ፤ በዞኑ ካለው ከ4 ሺህ ሄክታር በላይ የእርድ ማሳ፣ በዓመት ከ20 ሺህ ቶን በላይ ምርት ለማዕከላዊ ገበያ እንደሚቀርብ ተናግረዋል። ማዕከሉ የተሻሻሉ ዝርያዎችን ከማቅረብ ባለፈ፣ የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን ማስተዋወቁ ትልቅ ፋይዳ ያለው በመሆኑ፤ አርሶ አደሮች ተደራጅተው ማሽኑን መጠቀም የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። አስተያየታቸውን የሰጡ አርሶ አደሮችም፤ ነባሩ የእርድ ዝግጅት ሂደት የማገዶ፣ የውሃ እና የጉልበት ብክነት ስለሚያስከትል እስካሁን ከምርቱ ተገቢውን ጥቅም እንዳላገኙ ገልጸዋል። በተጨማሪም የተቀቀለው እርድ ደርቆ ለገበያ እስኪበቃ ረጅም ጊዜ ይወስድ እንደነበር አስታውሰው፤ ማዕከሉ ያስተዋወቀውን ማሽን በመጠቀም ምርታቸውን በቀላሉ አዘጋጅተው ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለገበያ ለማቅረብ ትልቅ ተስፋ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። የእርድ ምርት ለምግብ ዝግጅት፣ ለአልባሳት ማቅለሚያና ለፊት መዋቢያዎች ግብዓት ሆኖ የሚያገለግል ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጥቅም ያለው የቅመማ ቅመም ዓይነት መሆኑ ይታወቃል።
ስፖርት
ነገሌ አርሲ እና ምድረ ገነት ሽሬ ነጥብ ተጋሩ
May 21, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 33ኛ ሳምንት ነገሌ አርሲ እና ምድረ ገነት ሽሬ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ተካሄዷል። ጨዋታውን ተከትሎ ነገሌ አርሲ በ52 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ነገሌ አርሲ የሁለተኝነት ደረጃን ከመቻል የመረከብ እና ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት የማጥበብ እድል አልተቀመበትም። ምድረ ገነት ሽሬ በ37 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ዛሬ አስቀድመው በተደረጉ የ33ኛ ሳምንት ጨዋታዎች የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና አርባምንጭ ከተማን 3 ለ 0 ሲረታ አዳማ ከተማ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 33ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ከኢትዮጵያ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች በኋላ ከግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ወሳኝ ድል ተቀዳጅቷል
May 21, 2026 103
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና አርባምንጭ ከተማን 3 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ መስፍን ታፈሰ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር የአርባምንጭ ከተማው ኤፍሬም ታምራት በራሱ ላይ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በ14 ጎሎች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን የሚመራው የሲዳማ ቡናው አጥቂ አቤል ያለው ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ወደ ህክምና ስፍራ ተወስዷል። ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሲዳማ ቡና በ58 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። ከተከታዩ መቻል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ አድርጓል። በሊጉም 16ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 14ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርባምንጭ ከተማ በ29 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሐ ግብር አዳማ ከተማ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ውጤቱን ተከትሎ አዳማ ከተማ በ39 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ40 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ33ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሐ ግብር ነገሌ አርሲ ከምድረ ገነት ሽሬ ምሽት 12 ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሊጉ ግርጌ ከሚገኘው አርባምንጭ ከተማ ጋር ይጫወታል
May 21, 2026 207
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል። ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከሲዳማ ቡና በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። አርባምንጭ ከተማ በ29 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ሲዳማ ቡና በ55 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈው አርባምንጭ ከተማ ማሸነፍ በሊጉ የመቆየት ተስፋውን ለማለምለም የሚያስችለውን ሶስት ነጥብ እንዲያገኝ ያደርገዋል። ባለፉት አራት የሊግ ጨዋታዎች ላይ ከድል የራቀው ሲዳማ ቡና ዛሬ ካሸነፈ ከተከታዩ መቻል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ ያደርጋል። ጨዋታው ለሁለቱም ቡድኖች ወሳኝ የሚባል ነው። በሌላኛው መርሐ ግብር ነገሌ አርሲ ከምድረ ገነት ሽሬ ምሽት 12 ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ነገሌ አርሲ በ51 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ምድረ ገነት ሽሬ በ36 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በ32ኛ ሳምንት በመቻል የ4 ለ 0 ሽንፈት ያስተናገደው ነገሌ አርሲ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ እና በዋንጫ ፉክክሩ ለመቆየት ሶስት ነጥብ ማግኘት ይኖርበታል። በተመሳሳይ በ32ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 ያሸነፈው ምድረ ገነት ሽሬ በዛሬው ጨዋታ ድል ከቀናው ከወራጅ ቀጠና ሊወጣበት የሚችልበት እድል ሊፈጠር ይችላል። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። አዳማ ከተማ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። አዳማ ከተማ በ38 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ39 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ32ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አዳማ ከተማ በፋሲል ከነማ የ3 ለ 1 ሽንፈት ሲያስተናግድ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 ረቷል። ጨዋታው ለሁለቱም ቡድኖች ከወራጅ ቀጠና ስፍራ ፈቀቅ ለማለት ወሳኝ የሚባል ነው። የዛሬ መርሐ ግብሮች ዋንጫ ለማንሳት እና ላለመውረድ በሚደረገው ፉክክር ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው።
አስቶንቪላ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን አነሳ
May 21, 2026 230
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በዩሮፓ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ አስቶንቪላ ፍራይበርግን 3 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሚገኘው ቲውፕራሽ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዩሪ ቲሊማንስ፣ ኢሚሊያኖ ቡንዲያ እና ሞርጋን ሮጀርስ የማሸነፊያ ጎሎቹን አሳርፈዋል። በጨዋታው አስቶንቪላ የተሻለ ብልጫ የወሰደ ሲሆን ተጨማሪ ጎሎችን የማስቆጠር እድሎችን መጠቀም አልቻለም። የአስቶንቪላ ደጋፊ የሆኑት የዌልስ ልዑል ዊሊያምስ ጨዋታውን በስታዲየም በመገኘት ተከታትለዋል። ውጤቱን ተከትሎ አስቶንቪላ የዘንድሮው የዩሮፓ ሊግ አሸናፊ ሆኗል። ቪላ እ.አ.አ በ1982 የዩሮፓ ካፕ (የአሁኑ ሻምፒዮንስ ሊግ) ካነሳ 44 ዓመታት በኋላ ሌላኛውን የአውሮፓ ክብር ተቀዳጅቷል። ቡድኑ እ.አ.አ በ1996 የሊግ ካፕ ዋንጫውን ካነሳ በኋላ የመጀመሪያ ዋንጫውን አሳክቷል። ስፔናዊው የአስቶንቪላ አሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ ከተለያዩ ክለቦች ጋር ዩሮፓ ሊግ ዋንጫን አምስት ጊዜ በማንሳት አዲስ ታሪክ ጽፈዋል። ኤምሬ "የዩሮፓ ሊግ ንጉስ" የሚል የክብር ስም ተሰጥቷቸዋል። የዩሮፓ ሊግ አሸናፊው አስቶንቪላ በሊጉ አምስተኛ ደረጃን ይዞ ካጠናቀቀ በቀጣዩ ዓመት በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሚሳተፉ የእንግሊዝ ክለቦች ብዛት ወደ ስድስት ያድጋል። ፍራይበርግ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫ የማንሳት ህልሙ ሳይሳካ ቀርቷል።
አካባቢ ጥበቃ
በክልሉ ከ261 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ ችግኞችን ለመትከል የ ጉድጓድ ቁፋሮ ስራ ተጀምሯል
May 20, 2026 454
ባህርዳር ፤ግንቦት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከ261 ሺህ ሔክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ ችግኞችን ለመትከል የጉድጓድ ቁፋሮ ስራ መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንደገለፁት የክልሉን የደን ሽፋን ቀድሞ ወደ ነበረበት ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ነው። በመጭው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ የዋንዛ፣ ወይራ ፣ ዝግባ ፣ ፅድ ፣ አኬሺያ ዲከረንስ፣ ባህር ዛፍ፣ የፍራፍሬና ሌሎች ችግኞችን ለመትከል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የችግኝ ተከላውን በስኬት ለማከናወን እስካሁን 401 ሚሊዮን በላይ ጉድጓዶችን በማስቆፈር ለተከላ ዝግጁ ማድረግ መቻሉን አረጋግጠዋል። በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ ግብን ለማሳካት ተጨማሪ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶችን የማስቆፈር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። ባጠቃላይ በክረምቱ ለሚካሄደው ችግኝ ተከላ 261 ሺህ 297 ሄክታር መሬት ከወዲሁ ተለይቶ የጉድጓድ መቆፈር ስራው እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን የሰከላ ወረዳ አርሶ አደር መኮነን ልንገር እንደገለጹት ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር መጀመሩ ተራቁተው የነበሩ አካባቢዎችን መልሰው በደን እንዲሸፈኑ ለማድረግ አስችሏል። መርሃ ግብሩ ለመኖ ፣ በንብ ማነብና እንስሳት እርባታ እያስገኝ ያለውን ተጠቃሚነት ለማስፋት በመጭው ክረምት በሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በግልና በወል ቦታዎች ችግኝ ለመትከል ጉድጓዶችን እያዘጋጀን ነው ብለዋል። የሚተከሉት ችግኞች አያስገኙ ያለውን ጠቀሜታ በመረዳት በየዓመቱ ችግኞችን እያለማሁ ነው ያሉት ደግሞ በደቡብ ጎንደር ዞን የደራ ወረዳ አርሶ አደር ካሴ መንግስት ናቸው። በመጭው ክረምት የሚተከሉ ችግኞች ተንከባክበን በማሳደግ ለውጤት ለማብቃት ከወዲሁ ዝግጅት ጀምረናል ነው ያሉት። ባለፈው ክረምት በነቃ የህዝብ ተሳትፎ ከተተከለው ከአንድ ነጥብ አራት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥ 80 በመቶ የሚሆነው መጽደቁን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በአፍሪካ የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ለመከላከል ሀገራት ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል
May 19, 2026 620
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በአፍሪካ የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ለመከላከል ሀገራት ቅንጅታዊ አሰራራቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ፀባይ ትንበያ ማዕከል ጋር በመተባበር ለሁለት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየውን 73ኛውን የምስራቅ አፍሪካ የአየር ፀባይ አዝማሚያ ትንተናና ትንበያ ፎረም ተጠናቋል። በፎረሙ የቀጣናው ሀገራት ተወካዮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አጋር ድርጅት ተወካዮች እና ሌሎች አካላት ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና በዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዚዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ባለፉት ሁለት ቀናት በአፍሪካ ቀንድ ዙርያ ያሉ የኢጋድ አባል ሀገራት ያለፈው የበልግና መጪው ክረምት ወቅት የሚጠበቀውን የአየር ጠባይ ትንበያን አስመልክቶ ተወያይተዋል። በዚህም ሁሉም ሀገራት ከራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ በመነሳት የራሳቸውን የሜቲዎሮሎጂ መረጃዎችንና ከአካባቢያቸው አየር ሁኔታ በማገናዘብ ትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቅያ የሚሰጡበት ሁኔታ ላይ መነጋገራቸው አንስተዋል። ከአየር ትንበያው በመነሳትም የሚኖረው የአየር ሁኔታ በግብርና፣በውሃ፣በጤና ላይ ሊያደርሰ የሚችለው አሉታዊና አዎንታዊ ተፅእኖ በመገምገም ለቀጣይ ዝግጅት የሚደረግበት መሆኑ ተናግረዋል። እንዲሁም በህይወትና በንብረት ላይ ሊደርስ የሚችለውን የአደጋ ተጋላጭነትን ከመቀነስ አንፃር ጉልህ ድርሻ ያለው በመሆኑ መሰል መድረክ መዘጋጀቱ ጠቀሜታው የላቀ ነው ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚያጋጥሙ አደጋዎች በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ አደጋ እያደረሰ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ይህን ለመከላከል ሀገራት በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና የመተግበሪያ ማዕከል(ICPAC) ዋና ዳይሬክተር አብዲ ፊዳር (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የኢጋድ አባላት ሀገራት መረጃን መሰረት ያደረገ መረጃ በመለዋወጥ በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳሰበዋል።
ለዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ እስካሁን ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ችግኝ ተዘጋጅቷል-ግብርና ሚኒስቴር
May 19, 2026 535
አዲስ አበባ፤ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ለዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እስካሁን ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ችግኝ የማዘጋጀት ስራ መከናወኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ተፅዕኖን በመቀነስና የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ ዘርፈ-ብዙ ፋይዳዎችን እያስገኘ ይገኛል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የሀገር በቀል እጽዋቶችንና የተፈጥሮ ሀብቶችን ከመጠበቅ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅእኖ ለመከላከልና የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ መንግስት የተለያዩ ተግባራትን ከማከናወን አንጻር ግንባር ቀደም ለውጥ አስገኝቷል፡፡ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተሰሩት ስራዎች አበረታች ውጤት የተመዘገበ ሲሆን፤ በመርሃ-ግብሩ 48 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል የሀገሪቱን አረንጓዴ ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል። የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ልማት ከተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ባለፈ ዘርፈ-ብዙ ጥቅሞችን የሰነቀ ሲሆን የአየር ንብረት ተጽዕኖን በመቀነስ ለኢትዮጵያ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ እያስገኘ ይገኛል፡፡ ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ ለሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ዝግጅት በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ የግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፋኖሴ መኮንን ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ባለፉት ሰባት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ ላይ የተከናወኑ ሥራዎችና የተመዘገቡት አበረታች ውጤቶች ትልቅ ምስክር ናቸው፡፡ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሁለተኛው ምዕራፍ ማጠናቀቂያ መሆኑን የገለጹት መሪ ሥራ አስፈጻሚው፤ ቀደም ሲል ከነበሩ የአረንጓዴ አሻራ አፈጻጸሞች የተወሰዱ ተሞክሮዎችን መነሻ በማድረግ የዘንድሮው ዕቅድ በቁጥር ደረጃ ከፍ ያለ መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም መሠረት 8 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ ተይዞ ሰፊ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውንና አሁን ላይ ለተከላው የሚያስፈልጉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ ጠቁመው የስነ-ምህዳር ሁኔታን መሠረት ያደረገ የችግኝ ዝርያዎች መረጣ መከናወኑንም ጠቅሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ችግኝ የሚተከሉባቸው ጉድጓዶችን የማዘጋጀት ሥራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አሁን ላይ በበርካታ ዜጎች ዘንድ ባህል እየሆነ መምጣቱንና የተሳታፊዎች ቁጥርም ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አንድነት በተግባር የሚረጋገጥበት ትልቅ አገራዊ ኩነት በመሆኑ፣ መላው ሕዝብ በኃላፊነት ስሜትና በቀዳሚነት እየተሳተፈበት ይገኛል ብለዋል። ለዘንድሮው የችግኝ ዝግጅት ከተከናወኑ ሥራዎች መካከል 40 በመቶው ሀገር በቀል የደን ዛፎች ላይ ትኩረት ማድረጉን ጠቅሰው፣ 60 በመቶው ደግሞ ለምግብ ዋስትናና ለሌሎች ዘርፈ-ብዙ ጥቅሞች የሚውሉ የፍራፍሬና የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መሆናቸውን አስረድተዋል።
ትውልዱ የአካባቢውን ልምላሜ ጠብቆ በማቆየት የማህበረሰቡን የደን ልማት ባህል ማስቀጠል አለበት-የሀገር ሽማግሌዎች
May 19, 2026 461
ጂንካ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ትውልዱ የአካባቢውን ልምላሜ ጠብቆ በማቆየት የማህበረሰቡን የደን ልማት ባህል ለማስቀጠል ግንዛቤን እየፈጠሩ መሆኑን የአሪ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአሪ ማህበረሰብ ደኖችን ጠብቆ የማቆየትና የመንከባከብ ጠንካራ ባህል አለው። በዞኑ ሰሜን አሪ ወረዳ የጎዛ ቀበሌ የሀገር ሽማግሌዎችም ትውልዱ የአካባቢውን ልምላሜ ጠብቆ በማቆየት ለመጪው ትውልድ እንዲያሻግር ግንዛቤ በመፍጠር ደኖችን የመንከባከብ ባህሉን ለማስቀጠል እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የሃገር ሽማግሌ አቶ ተክሌ ተረፈ እንደገለፁት፤ በአካባቢው ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሻገር የቆየ ደኖችን የመንከባከብ እና ጠብቆ የማቆየት ባህል አለ፡፡ ባህሉ ሳይሸራረፍ እንዲቀጥል በደን ተከላና እንክብካቤ ከማሳተፍ ባለፈ የደኖች መኖር ያለውን ጠቀሜታ በተመለከተ ግንዛቤ የመስጠትና የማስተማር ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። በእርሻ ስራ ውጤታማ ለመሆን ደኖችን ጠብቆ ማቆየት ተገቢ መሆኑን ጠቁመው ደን ከሰው ልጅ ህይወት ጋር ጥብቅ ቁርኝት ስላለው እንክብካቤ እንደሚያስፈልገውም አስረድተዋል። ደኖች የተራቆቱባቸው አካባቢዎች በተፈጥሮ አደጋዎች በተደጋጋሚ ሲፈተኑ አስተውለናል ያሉት ደግሞ የሀገር ሽማግሌው ብላታ ቶዳ ናቸው። አዲሱ ትውልድ ይህን በመገንዘብ ደኖችን እንዲንከባከብ፣ በተራቆቱ አካባቢዎች ችግኞችን እንዲተክሉ ግንዛቤ በመፍጠር ትውልዱን የማነፅ ስራ እየሰሩ እንደሚገኙም ገልጸዋል። የአሪ ባህላዊ የዕርቅ ስነ-ስርዓት፣ አፈ-ታሪኮች፣ የመጪው ዘመን ትንበያ እና ሌሎች ባህላዊ ስነ-ስርዓቶች የሚፈፀሙት በደኖች አካባቢ በሚገኝ ትልቅ ዋርካ ስር እንደሆነ የገለፁት ደግሞ አቶ አለማየሁ ታጋ ናቸው። በደኖች አካባቢ የሚፈፀሙ ባህላዊ ስርዓቶች የደኖችን ጥቅም ለአዲሱ ትውልድ ለማስተማር ታስቦ እንደሆነም አመልክተዋል። ደኖች ከሰው ልጅ ህልውና ጋር የተቆራኙ በመሆናቸው አዲሱ ትውልድ ይህን ተገንዝቦ የአካባቢውን ለምላሜ ጠብቆ እንዲያቆይ የማስተማር ስራ እየሰራን ነው ብለዋል። በአሪ ዞን የአካባቢ ጥበቃ እና የአየር ንብረት ለውጥ ጽህፈት ቤት የደን ጥበቃና ቁጥጥር የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ክንዴ ፍሰሃ በዞኑ ደኖችን ጠብቆ ለትውልድ የማሻገር ጠንካራ ባህል እንዳለ ገልፀዋል። በዞኑ ከ21 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት በደን መሸፈኑን ጠቁመው በዚህም 41 ጥብቅ የተፈጥሮ ደኖች እንደሚገኙ ተናግረዋል። በአካባቢው በሚገኘው ደን ውስጥም ለመድኃኒትነት የሚያገለግሉ በርካታ የዕፅዋት ዓይነቶች እንዳሉም አስረድተዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዞኑ ከ12 ሚሊዮን በላይ ችግኞች በተራቆቱ አካባቢዎች የሚተከሉ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅትም የአካባቢው የደን ሽፋን እያደገ መምጣቱን አብራርተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 1655
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 1008
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 930
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በአዲስ አበባ ይካሄዳል
May 13, 2026 972
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በሕብረቱ ዋና መቀመጫ ዛሬ በአዲስ አበባ ይደረጋል። በውይይቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እንደሚገኙ ይጠበቃል። ውይይቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል በአፍሪካ ልማት እና በዓለም አቀፍ አስተዳደር ዙሪያ ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ቅንጅት፣ የጋራ ተጠያቂነት እና ትብብርን በልማት፣ በአስተዳደር፣ በሰብአዊ ድጋፍ እና በሰላም ግንባታ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ያላቸውን ትስስር ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ይካሄዳል። በዚህ የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ላይ በርካታ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች የሚዳሰሱ ሲሆን፣ በተለይም የአጀንዳ 2063 እና የሁለተኛው የአስር ዓመት ምዕራፍ የትግበራ ዕቅድ አፈፃፀምን ማፋጠን እንዲሁም አፍሪካን በዓለም አቀፍ ፖሊሲ እና አስተዳደር ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና መጠበቅ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል። በተጨማሪም "ከጥገኝነት ወደ ሉዓላዊነት" የተሸጋገረ የልማት ፋይናንስ፣ የ2026 የአፍሪካ ሕብረት የዓመቱ መሪ ቃል የሆነው ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና የንጽህና አጠባበቅ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ተቋማት ሪፎርም እና አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ያላትን ውክልና የተመለከቱ ጉዳዮች ውይይት ይደረግባቸዋል። መድረኩ ለአህጉራዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔዎችን ማምጣት፣ የአገር ውስጥ ሀብት ማሰባሰብን ማሳደግ፣ የወጣቶች እና የሴቶች ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዲሁም በአህጉራዊ እና በዓለም አቀፍ የልማት የቅድሚያ ትኩረቶች መካከል ያለውን ትስስር ማጠናከር ወሳኝ መሆኑ አጽንኦት የሚሰጥበት እንደሆነ ተመላክቷል። ከውይይቱ ከሚጠበቁ ውጤቶች መካከል የተሻለ ስትራቴጂካዊ ቅንጅት፣ ፍትሐዊ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ፣ በአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ቃል ዙሪያ ጠንካራ ቅንጅት መፍጠር እና በተባበሩት መንግሥታት ሥርዓት ውስጥ ፍትሐዊ የአፍሪካ ውክልና እንዲኖር የቀረቡ ጥሪዎችን ማጠናከር እንደሚገኙበት ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የውይይቱን ውጤቶች አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ይሰጣሉ።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 972
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 1557
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 1379
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች
May 3, 2026 1447
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር እያሸጋገራት ይገኛል።የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የመሰረተ ልማት እና የተቋማት ግንባታ ስራዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋንኛ ስራዎች ናቸው። ለውጡን ተከትሎ መንግስት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን ስትራቴጂ በመቅረጽ የዲጂታላይዜሽን ስራውን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶ አድርጎታል። የለውጡ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ ቴክኖሎጂን እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመቁጠር "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን አጠቃላይ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ተግባር ገባ።ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱን የዲጂታል ጉዞ ከመሰረቱ የለወጠ ሲሆን፣የመጀመሪያው ትልቅ እርምጃም የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ነበር። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ የኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል።በተለይም የአምስተኛ ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን አስችሏታል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ለውጡ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ውጤት አምጥቷል።እንደ ቴሌብር (telebirr) ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ምንም የባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ፣ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር ትልቅ መደላድል ፈጥረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ አድማስ ይበልጥ አስፍተውታል። የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ራዕይ ለዓለም ያሳየችበት አጋጣሚ ነው።ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የካንሰር ህመምንና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ መለየት የሚያስችሉ የኤአይ ውጤቶችን አበልጽጓል። በግብርናውም ረገድ የአፈርን ለምነትና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ዋስትና ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል ዓለም ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የፋይዳ (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን መረጃ በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የለውጡ ፍሬያማነት ማሳያ ነው።የሳይንስ ሙዚየምም የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያሳይና የሀገሪቱን ቴክኖሎጂ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ሆኗል።የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቅርቡ መጠናቀቁ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2025 ስትራቴጂው መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዲጂታል 2030ን ይፋ ሲያደርጉ የነበረው ትልቁ መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች የሚል ነው። ስትራቴጂው በዋናነት"የፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት፣ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠር፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) አድርጎ መገንባትን እንደ ዋነኛ ግብ አስቀምጧል። ይህም ሁሉን አቀፍ የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ የመንግስት አገልግሎቶችን መቶ በመቶ ወረቀት አልባ በማድረግ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) በግብርና፣ በጤናና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ በስፋት በመተግበር የምርታማነት አብዮት መፍጠርን ያለመ ነው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ስራ በአህጉራዊ ደረጃ ያለውን ተቀባይነትና የተሰጣትን ትልቅ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት የቴክኖሎጂ ከፍታ፣ ሀገሪቱን በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ተፎካካሪ ብቻ ሳይሆን የፈጠራ ምንጭ እንድትሆንም እያደረጋት ይገኛል። በዚህ ረገድም የቀጣዩ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ስኬትም ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና በቴክኖሎጂ የበለጸገች ሀገር የማድረግ ራዕይን ለማሳካት እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ ያገለግላል።
ትንታኔዎች
እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት
May 17, 2026 3307
በኢዜአ ዐይን …! በዮሐንስ ደርበው እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉን የሚሉ እሮሮዎች በተለያዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሲነሱ ቆይተዋል። በተለይም በአንዳንድ ተቋማት መንግሥታዊ አገልግሎት ለማግኘት እዚያም እዚህም መንከራተት፤ደግሞም ወረፋ በመጠበቅ መጉላላት ብሎም ለጊዜና ገንዘብ ወጪ መዳረግ ይስተዋላል የሚሉ ሐሳቦች ተስተጋብተዋል። ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ባሳለፍነው ሳምንት … መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል አሠራር በመንደፍ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ አስጀመረ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማዕከሉ አገልግሎት ባስጀመሩበት ወቅትም ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው ብለው ነበር። አሁን ላይም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ነው።መስፋፋቱም በማዕከላት ብዛት፣በአገልግሎት መስጫ መስኮቶች ቁጥር እና በአገልግሎት ዐይነቶች እየተገለጠ ነው። በዚህም በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት የተደራጁ ሲሆን ይህ አሃዝም ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እና ያለውን ፈጣን እድገት ያመላክታል። ጉዳዩ የዜጎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ማላቅ፤ ብልሹ አሠራርንም መቅረፍ ነውና መንግሥት በልዩ ትኩረት ይዞታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ አሥተዳደርና በሐረሪ ክልል ጉብኝት ባደረጉበት ወቅትም፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የምልከታቸው አካል ማድረጋቸው ለጉዳዩ የተሰጠውን ከፍያለ ትኩረት ያሳያል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሶብ የሞባይል አገልግሎትን በመረቁበት ወቅት ደግሞ፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ብለዋል። አክለውም፤በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች ዕርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል፤ ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፤ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ መሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል ማለቱም ይታወቃል። የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ደግሞ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ ያስቻለ ስኬት ተገኝቷል ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ የመንግሥት አገልግሎቶችም ዜጋ ተኮር፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አብራርተዋል። በዲጂታል 2030 የአገልግሎት አሰጣጥ አመላካች ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚጠቀሱ 50 ሀገራት መካከል አንዷ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ዜጎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በኦንላይን በየትኛውም ቦታ ሁሉንም አገልግሎቶች እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ ስለመሆኑም እንዲሁ። አገልገሎቱን ያገኙ አስተያየት ሰጭዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ እንግልትን ያስቀረ፣ ጊዜና ወጭን የቀነሰ ነውና ይስፋፋ፤ ተጠናክሮም ይቀጥል። #መሶብ_የአንድ_ማዕከል_አገልግሎት #የዜጎችን_እንግልትና_ብልሹአሠራርን_መቅረፍ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #በኢዜአ_ዐይን
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 17, 2026 1652
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 2 እስከ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ጋር መምከራቸው ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም በኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል። ለነበረን ጠቃሚ የሐሳብ ልውውጥና ቀጣይነት ላለው አጋርነትም ምስጋናዬ የላቀ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ በኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና በፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በጋራ አዘጋጅነት በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካፍለዋል። በዚሁ ወቅትም በተለይም የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት እና የኃይል ሽግግርን በተመለከተው ውይይት ላይ ከተሞክሯችን የተቀዱ ከፍ ያሉ ሐሳቦች ተነስተዋል ብለዋል። አክለውም፤ ኢትዮጵያ በተነሱት ሁለት ዘርፎች የጀመረችውን ሥራ በማጠናከር የላቀ ሚና መጫወቷን ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንኳን ደህና መጡ ስል ሁልጊዜም በልዩ ኩራትና ደስታ ነው ሲሉ ተቀብለዋቸዋል። ከአቀባበሉ በኋላም፤ መሪዎች በጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በዚህም መሠረት፤ በታዳሽ፣ የተቀናጀ እና ዘላቂ ኃይል እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራምን ለመተግበር የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ ብድርን ጨምሮ የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የመንግሥትና የግል አጋርነት አዲስ የማዕቀፍ እና የፍኖተ ካርታ ስምምነት ተፈርሟል። · ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ማውጣቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርገዋል። እነዚህ አራት ቴምብሮች እ.ኤ.አ. በ1945 በሳን ፍራንሲስኮ የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን ከመፈረም ጀምሮ፤ በኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን እስከማሰማራት እና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ እስከ ማስተናገድ ያለውን የጋራ ታሪካችንን የሚተርኩ ናቸው ብለዋል። በዓለም የፖስታ ኅብረት በኩል ለ192 ሀገራት የተሰራጩት እነዚህ ቴምብሮች፤ ለአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን ለትውልድ ሁሉ የሚተርፍ የታሪክ ዐሻራ ማሳያ መሆናቸውንም አስታውቀዋል። በተያያያዘም፤ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ በዘመናዊው ታሪክ ውስጥ እጅግ ፈታኝ በሆነ ወቅት ላይ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር ጥልቅ አድናቆታችንን እንገልጻለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የተባበሩት መንግሥታት የጸናው ሀገራት ከመከፋፈል ይልቅ ውይይትን ስለመረጡ መሆኑን አስገንዝበው፤ ኢትዮጵያም ይህንኑ የሁልጊዜ ምርጫዋን ታጸናለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም የምክክር ባህል እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበው፤ ጠንካራ የሲቪክ ማኅበረሰብ ባህል ግንባታ ደግሞ ያላሰለሰ የመነጋገር ልምምድ እና የሰከነ የወል መደማመጥን ግድ ይላል ብለዋል። የእስካሁን ሂደቱም በማኅበረሰባችን በየደረጃው የመደማመጥን ከፍ ያለ ጠቀሜታ አሳይቷል ሲሉም ገልጸዋል። ሂደቱ በሀገራችን ሁሉም ማዕዘናት የሚገኙ ከ90 በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን አመለካከቶች እና የውይይት ውጤቶች ያንፀባረቀ ሆኗልም ነው ያሉት። ለሀገር ወሳኝ ፋይዳ የያዘው የምክክሩ ምዕራፍ ተጨባጭ ውጤት ወደሚያስገኘው ቀጣይ ምዕራፍ በሚሸጋገርበት በዚህ ወቅት፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለሀገራችን ሰላም፣ አንድነት እና ዘላቂ መረጋጋትን የሚያረጋግጥ የጋራ ፅኑ አቋም እና ገንቢ በሆነ መንገድ አስተዋፅኦ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል። · የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን በመረቁበት ወቅት፤ ፓርኩ አስተማማኝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጀመርነው የብልጽግና ጉዞ ተደማሪ እመርታ ነው ብለዋል። ለመካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች ምቹ የንግድ ከባቢ ከመፍጠር ባሻገር በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶቻችን የሥራ ዕድል ይከፍታል ሲሉም ገልፀዋል። ፓርኩ የሀገራችን አምራቾች አቅማቸውን በማጎልበት፣ ምርታማነታቸውን ማሳደግና ተወዳዳሪነታቸውን በመጨመር ለከተማችን፣ ለሀገራችንና ለቀጣናው የሚተርፉበት ታላቅ እድልን ይዟል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተኪ ምርቶችን በማምረት በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛና ቀልጣፋ የንግድ ትስስር ይፈጥራል፤ ምርቶችን ደግሞ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይጫወታል ሲሉ አስረድተዋል። · ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ መጀመር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔን ባስጀመሩበት ወቅት፤ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ቆራጥ ጥረት ውስጥ የሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል በማድረግ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በመላ ሀገሪቱ ከ35 ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት የነጻና አስገዳጅ ትምህርት ተደራሽ እንዲሆን እያደረግን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር ላይ መሥራት በመሆኑ ተባብረን፣ በጊዜ የለንም መንፈስና በትጋት እንሥራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። · የፖሊሲ ቀን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ ባሳላፍነው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው የፖሊሲ ቀን ተከብሯል። በዚሁ ወቅትም፤ ውጤታማ ፖሊሲ ለሀገራዊ ዕድገት የጀርባ አጥንት መሆኑን አስገንዝበው፤ መንግሥት በግልፅ፣ ተተግባሪና ጥራት ባላቸው ፖሊሲዎቹ ለሕዝብ የገባውን ቃል እየተገበረ ስኬትም እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ሀገራችን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ በጂኦ-ፖለቲካዊና በቴክኖሎጂ ለውጦች ላይ ቀድሞ ምላሽ የሚሰጡ ጥናቶች ያስፈልጋሉ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በዕውቀት ላይ ኢንቨስት በማድረግ እና ለማስረጃዎች ዋጋ በመስጠት፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ የፖሊሲ ሥነ-ምኅዳር ለመገንባት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ለዚህ ስኬት ሁላችንም በጋራ እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
የጤና ነገር
May 15, 2026 1475
በዮሐንስ ደርበው ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ሾተላይ የሚከሰተው RH-Negative የሆነች እናት RH-Positive የሆነ ፅንስ በምታረግዝበት ወቅት የእናትየው በሽታ የመከላከል ሥርዓት የፅንሱን ደም እንደ ባዕድ ነገር በመቁጠር በሚያመነጨው ንጥረ-ነገር (Antibodies) አማካኝነት መሆኑን የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። የጽንስና ማህጸን ስፔሻሊስት ዶክተር ዳንኤል ኃብተማርያም ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ከወሊድ ጋር በተያያዘው አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ወይም ሾተላይ እየተባለ በሚጠራው በጽንስ ላይ የሚያጋጥም ችግር ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሾተላይ ወይም አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ዳንኤል ማብራሪያ፤ ሰዎች ከሚታወቁበት አራቱ የደም ዓይነቶች ምደባ (ኤ፣ ቢ፣ ኤቢ እና ኦ) በተጨማሪ በቀይ ደም ኅዋስ ሰርፌስ ላይ በፕሮቲን መኖርና አለመኖር ይለያሉ። በዚህም መሠረት አር ኤች ፖዘቲቭ (RH+) እና አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ተብለው እንደሚከፈሉ ያስረዳሉ። በዚህ ምደባ መሠረት ከአጠቃላይ ሕዝቡ 85 በመቶው አር ኤች ፋክተር ፖዘቲቭ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ማለት በቀይ ደም ኅዋሳቸው ሰርፌስ ላይ ፕሮቲን አላቸው ማለት ነው ይላሉ። 15 በመቶው ደግሞ አር ኤች ኔጌቲቭ ወይም በቀይ የደም ኅዋሳቸው ሰርፌስ ላይ ፕሮቲን የሌላቸው ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። አክለውም አር ኤች ኔጌቲቭ ወይም ፖዘቲቭ መሆን በሽታ እንዳልሆነ በአጽንኦት ገልጸው፤ ከወላጆች የሚወረስ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ አንድ ልጅ ሲወለድ እንደ ወላጆቹ አር ኤች ፋክተር መሠረት አር ኤች ፖዘቲቭ ወይም አር ኤች ኔጌቲቭ ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። ይህን በምሳሌ ሲያስረዱም፤ አንዲት ሴት አር ኤች ፋክተሯ ኔጌቲቭ ሆኖ ጽንሷ ደግሞ አር ኤች ፖዘቲቭ ቢሆን ተገቢው የሕክምና ክትትል ካልተደረገ ብሎም የእናትና ልጅ ደም ንክኪ ከተፈጠረ የበሽታ መከላከል ሥርዓቷ የሚያመነጨው አንቲ ቦዲ ጽንሱን እንደ ባዕድ ነገር ስለሚቆጥረው ጉዳት (ሾተላይ) ያስከትላል ይላሉ። የአንቲ ቦዲ ሥራ ሴቷ ለአር ኤች ፖዘቲቭ የምትጋለጥበት ሁኔታ ከተፈጠረ ጽንሱን (አር ኤች ፋክተሩ ከእሷ ተቃራኒ ሲሆን) እንደ ባዕድ ነገር ቆጥሮ ሴትዮዋን ለመከላከል በጽንሱ ላይ ጥቃት ማድረስ መሆኑንም አመላክተዋል። መፍትሔው ምንድን ነው? ለማንኛውም ጤናማ የእርግዝና ሂደት የሕክምና ክትትል ማድረግ ቀዳሚ መፍትሔ መሆኑን መክረዋል። ከሾተላይ ጋር በተያያዘ ደግሞ በእርግዝና ወቅት የሚስትና ባልን አር ኤች ፋክተር መለየት ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህን ተከትሎም አር ኤች ፋክተራቸው ተመሳሳይ ከሆነ ጽንሱም ከእነሱ ጋር ስለሚመሳሰል ጤናማ እንደሚሆን ገልጸዋል። በአንጻሩ ግን፤ አር ኤች ፋክተሯ ኔጌቲቭ የሆነች ሴት የባለቤቷ አር ኤች ፋክተር ፖዘቲቭ ከሆነ ወይም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ ሰውነቷ መከላከያ አምርቷል ወይስ አላመረተም የሚለው በሕክምና ምርመራ እንደሚታወቅ አስረድተዋል። ይህ ምርመራ ሲሠራ ውጤቱ ኔጌቲቭ ከሆነ ወይም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ ሰውነቷ መከላከያ አላመረተም የሚል ከሆነ በዚህኛው እርግዝናም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ፣ የእናትና የጽንስ ደም ንክኪ ኖሮ መከላከያ እንዳታመርት የሚሰጥ ሕክምና እንዳለ አረጋግጠዋል። ይህ ሕክምናም 28ኛ ሳምንት ላይ በመርፌ ለመጀመሪያ ጊዜ ይሰጣል ብለዋል። ከወለደች በኋላ ደግሞ የተወለደው ልጅ አር ኤች ፋክተር ታይቶ እንደእናቱ ከሆነ ተጨማሪ መድኃኒት እንደማያስፈልግና ከአባቱ ጋር ከተመሳሰለ ግን (አር ኤች ፖዘቲቭ ከሆነ) በመርፌ ተጨማሪ መድኃኒት በወለደች በ72 ሠዓት ውስጥ በመስጠት ለቀጣይ እርግዝናዎች ሰውነቷ መከላከያ እንዳያመነጭ ማድረግ እንደሚቻል አብራርተዋል። በሌላ በኩል ከሾተላይ ጋር በተያያዘ የሚደረጉ ሳይንሳዊ ያልሆኑ ልማዳዊ ድርጊቶችን ኮንነው፤ ትክክለኛው መፍትሔ ያለው የሕክምና ክትትል በማድረግ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲሁም፤ በተለይም የጎንዮሽ ህመም ያለባቸው ሴቶች (የኩላሊት፣ የደም ግፊት፣ ስኳር እና ሌሎችም) ቀድመው ሐኪም አማክረው ወደ እርግዝና ቢገቡ እንደሚመከር ገልጸው፤ የቅድመ እርግዝና ክትትል ማድረግ ካልተቻለ እንኳን በእርግዝና ወቅት በአግባቡ ክትትል ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል። ለመከላከያ ትልቅ ትኩረት መስጠት ችግሩ ተፈጥሮ ከመታከም የተሻለና ተመራጭ መፍትሔ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። #የጤና_ነገር #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት
ለተቃና ነገ የኢትዮጵያ ትጋት አንዱ መገለጫ
May 11, 2026 2126
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ ከምትከውናቸው ዐበይት ጉዳዮች መካከል ሰው ተኮር ተግባራት ቀዳሚው ነው። በአዲስ አበባ በተካሄደው ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ጥረት ሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ ነው ብለዋል። መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል አድርጎ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በዚህም መሠረት፤ የልጆች ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት፣ የምገባ ሥርዓትን ማሳደግ፣ የሕጻናት መጫወቻ ሥፍራዎች ግንባታ ላይ ተጨባጭ ውጤቶች መምጣታቸውንም ነበር የጠቀሱት። ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማትና ትምህርት ፖሊሲ የዘላቂ ብልጽግና መንገዳችን ከሆነው የመደመር ዕሳቤ ጋር በተናበበ መልኩ እየተተገበረ በስኬት ቀጥሏልም ብለዋል። ኢትዮጵያ ለነገ የተዘጋጀ ትውልድ ለመገንባት በሕግና በፖሊሲ የተደገፉ የቀዳማይ ልጅነት ኢኒሼቲቮችን እየተገበረች እንደምትገኝም አስታውቀዋል። ለአብነትም፤ በ2015 ተሻሽሎ የፀደቀው ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማት እና ትምህርት የፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲሁም በ2017 የፀደቀውን አጠቃላይ የትምህርት አዋጅ መሠረት በማድረግ ከ35ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላው ሀገሪቱ እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል። በመንግሥት ተቋማት የሕጻናት ማቆያ ማዕከላት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በመጠቆምም፤ ኢትዮጵያ የሕጻናትን ደኅንነት ማሻሻል የሚያስችል ጉልኅ ብሔራዊ መርሐ-ግብር መጀመሯን አንስተዋል። በሰቆጣ ቃል ኪዳን አማካኝነት የ15 ዓመት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ ከሁለት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ላይ የሚደርሰውን መቀንጨር በ2022ዓ.ም ዜሮ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። የሌማት ትሩፋትና የአልሚ ምግቦች ምርታማነት የሕጻናትን ጉዳት ለመቀነስና የልጆችን ጤናማነት መጨመር እያስቻሉ እንደሚገኙም ነው የተናገሩት። ኢትዮጵያ ለዘላቂ የልማት ግቦችና ለሕጻናት መብቶች ጥበቃ የገባቻቸውን ቃል ኪዳኖች ወደ ተግባር እየለወጠች መሆኑን በማንሳት፤ ይህንንም አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። መንግሥት ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን በመላ ሀገሪቱ ለማስፋት ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑንም አመላክተዋል። በዚህም መሠረት፤ በጀት በመመደብ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል፣ የተማሪዎችን ምገባ በማስፋፋት ውጤት ማምጣቱን ነው የሚያብራሩት። ልጆች በአካልና በመንፈስ የሚጎለብቱባቸው የስፖርትና የመዝናኛ ቦታዎች በየአካባቢው በመገንባት፣ በኮሪደር ልማት ለልጆች ምቹ ሥፍራ እየተፈጠረ መሆኑንም በመጥቀስ። ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር፣ አኅጉር እና ዓለም ላይ መሥራት በመሆኑ በትጋት ማስቀጠል እንደሚገባም በአጽንኦት ይናገራሉ። አፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ተግዳሮቶችን ለመፍታት የራሷን መፍትሔዎች በማፍለቅ፣ በብሔራዊ የልማት አጀንዳዋ እያካተተች መሆኑን የሚገልጹት ደግሞ የአፍሪካ ቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ከበደ ወርቁ ናቸው። በሕጻናት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ማንኛውም ሀገር በመጪው ትውልድ ላይ ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው እጅግ አስፈላጊ ኢንቨስትመንቶች አንዱ መሆኑንም ያነሳሉ። አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ ያሉባትን ተግዳሮቶች ከመጋፈጥ ባለፈ፤ የራሷን መፍትሔዎች እያመነጨች መሆኑንና ጉዳዩን የብሔራዊ ልማት አጀንዳዋ አካል እያደረገችው እንደምትገኝም ገልጸዋል። አዲስ አበባ ይህን ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ እንድታስተናግድ የተመረጠችበት ዋና ምክንያትም፤ በዘርፉ እያከናወነች ያለው ተግባር አርዓያነት ያለው በመሆኑ ነው ብለዋል። ከተማዋ የጤና እና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎቶችን ያካተተ የተቀናጀ ዘርፈ-ብዙ አሠራር መዘርጋቷን ጠቅሰው፤ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት እና የቀን የሕጻናት እንክብካቤ ማዕከላትን በከተማ አቀፍ ስትራቴጂ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝም ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው፤ መዲናዋ በቀዳማይ ልጅነት ያመጣችው ተጨባጭ ውጤት በአርዓያነት እንድትጠቀስ እንዳደረጋት አንስተዋል። በሕጻናት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች፤ በትምህርት፣ በሰው ሃብት ልማትና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ፋይዳ እንዳለውም አስረድተዋል። በዚህም በአዲስ አበባ ፍትሐዊና አካታች የቀዳማይ ልጅነት ልማት መርሐ-ግብርን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ የትውልድ ግንባታ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል። "ሕጻናት የአዲስ አበባ የነገ ተስፋዎች" የሚል ፍኖተ ካርታ በመቅረጽ 1 ነጥብ 3 ሚሊየን ለሚሆኑ ከስድስት ዓመት በታች ሕጻናት ሁለንተናዊ ዕድገት መረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በትምህርት ቤት ምገባ መርሐ-ግብርም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ ዩኒፎርምና በቀን ሁለት ጊዜ ምግብ በማቅረብ በሕጻናት ክብካቤ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል ነው ያሉት። የሕጻናት ማቆያና መጫወቻ የመሠረተ-ልማት ግንባታ፤ ሕጻናት ነፃ የሕክምና፣ የምገባና የሥነ-ልቦና አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። የቀዳማይ ልጅነት መርሐ-ግብር በ2015 ዓ.ም ሲጀመር በዕድገት ወደ ኋላ የቀሩ የሕጻናት መጠን ከነበሩበት 13 በመቶ አሁን ላይ ወደ 10 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉን ከንቲባዋ አመላክተዋል። አክለውም፤ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዝግጁነታቸው ከነበረበት 49 በመቶ አሁን ወደ 90 በመቶ ማደጉንም ተናግረዋል። ሀገር በሁሉም ዘርፍ የበቃ መጪ ትውልድ እንዲኖራት መንግስት የያዘው ጥረት በሚፈለገው መጠን ለውጤት እንዲበቃ የሁሉንም ትኩረትና ተሳትፎ ይሻል። ለነገ በሁሉም ዘርፍ የዳበረ ትውልድና የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን ዛሬ ላይ እየተደረገ ያለው ርብርብ የሀገራችንን መፃኢ ብሩህ ተስፋ ይበልጥ የሚያለመልም ነውና ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 6531
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 4018
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 9809
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 8289
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 1289
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 2141
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።