ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በይርጋዓለም ከተማ የሌማት ትሩፋት መርሀግብር የዶሮ አርቢዎችን ኢኮኖሚያዊ አቅምን እያሳደገ ነው
Aug 19, 2026 111
ይርጋለም፤ ነሀሴ 13/2018 (ኢዜአ)፡-በይርጋዓለም ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዶሮ እርባታ ሥራ የተሰማሩ ማህበራት ከእንቁላል ምርታቸው ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ገለጹ። በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ይርጋዓለም ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ማህበራት እንደገለጹት፣ የተሰማሩበት የዶሮ እርባታ ሥራ የእንቁላል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ አቅማቸውን እያሳደገው ነው። ከእንቁላል ሽያጭ በሚያገኙት ገቢ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱንም ለኢዜአ ገልጸዋል።   ‎በከተማው የጌዶሴይ ዶሮ እርባታ ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ከተማ ካቢሶ ሥራውን በ1 ሺህ የእንቁላል ጣይ ዶሮዎች እንደጀመሩ አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ያሏቸው የዶሮዎች ቁጥር 4 ሺህ መድረሱን ተናግረዋል። ከእነዚህም በቀን ከ3 ሺህ 700 በላይ እንቁላል እንደሚሰበስቡና ከሽያጩም የተሻለ ገቢ እያገኙ መሆናችውን አስረድተዋል።   ከእንቁላል ምርት ባለፈ የአንድ ቀን ጫጩቶችን በማስመጣትና አሳድገው በ48 ቀናቸው ለተጠቃሚዎች በማስረከብ ተጨማሪ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ከመንግስት የመስሪያ ቦታ፣ የስልጠናና ሌሎች ድጋፎችን እያገኙ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።   የደረሰና ቤተሰቡ የዶሮ እርባታ ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረሰ አሰፋ በበኩላቸው "የዶሮ እርባታ ሥራ አስፈላጊ መኖና ሕክምናን ከማሟላት ባለፈ በጥንቃቄ መስራት ከተቻለ ትርፋማ ያደርጋል" ብለዋል። በአንድ ሺህ የእንቁላል ጣይ ዶሮዎች የጀመሩትን ሥራ አስፋፍተው በአሁኑ ወቅት ከ10ሺህ በላይ ዶሮዎች እንዳሏቸው ገልፀዋል፡፡ በቀን ከ9 ሺህ በላይ እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ደረሰ፣ በስራቸው ለሌሎቸም የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ነው የተናገሩት ከመንግስት ነጻ የዶሮ ክትባቶችን ጨምሮ የሙያና የተለያየ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም ገልፀዋል፡፡   የሲዳማ ክልል እንስሳት ሀብት ልማት ቢሮ ምክትልና የዝርያ ማሻሻልና መኖ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አደገ አለሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው በክልሉ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የዶሮ ልማት ሥራ ትልቅ እመርታ ማሳየቱን ገልጸዋል፡፡ የዶሮ ሀብት ልማት በየቤታቸው የተወሰኑ ዶሮዎችን የሚያረቡ አርሶ አደሮች፣ በማህበር ተደራጅተው የሚሰሩ ዜጎችን እንዲሁም በግል የሚያለሙ ባለሀብቶችን ተጠቃሚ አድርጓል ብለዋል። በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት እና ዶሮ ፈላጊዎች የዶሮ አቅርቦት፣ የሙያ እገዛና ሌሎች የድጋፍና ክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ኃላፊው አደገ (ዶ/ር) ጠቁመዋል፡፡ እንደእሳቸው ገለጻ ከአምስት ዓመት በፊት በክልሉ በዓመት ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በታች የነበረውን የዶሮ ሥርጭት በአሁኑ ወቅት 20 ሚሊዮን ለማድረስ ተችሏል። በተያዘው 2019 በጀት ዓመትም 24 ሚሊዮን ዶሮዎችን ለማሰራጨት ማታቀዱን ጠቁመዋል፡፡    
ቡሄ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ምስረታ ታሪካዊ ቁርኝት
Aug 19, 2026 97
በሙሴ መለሰ ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን የቡሄ በዓል በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ባለበት በዚህ ዕለት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አጀማመሩንና ምስረታውን ከዚህ በዓል ጋር ያለውን የጠበቀ ትስስር ወደ ኋላ መለስ ብሎ የሚታወስበት ነው። የክለቡ ምስረታና የቡሄ በዓል (የሆያ ሆዬ ጨዋታ) ቀጥተኛና የማይነጠል ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፣ ክለቡ በመስረታው ወቅት የነበረበትን የፋይናንስ እጥረት ቀርፎ የመጀመሪያውን ማሊያ ለመግዛት የበቃው በዚህ ዕለት በተሰበሰበ የሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ነበር። የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን መጀመሪያ ሲጠነሰስ በጆርጅ ዱካስና በአየለ አትናሽ አማካኝነት የነበረ ቢሆንም፣ ክለቡን በይፋ አደራጅቶ ለማቋቋም ግን የግድ የፋይናንስ አቅም ወይም ገንዘብ ያስፈልግ ነበር። ሆኖም ግን በሃገር ፍቅር ስሜት የተነሱት ዘጠኙ ወጣቶች ማለትም አየለ አትናሽ፣ ጆርጅ ዱካስ፣ ዮሐንስ ጥላሁን፣ ገብረመድህን ተፈሪ፣ ተፈራ ገብረእግዚአብሔር፣ ዓለማየሁ እጅጉ፣ መኮንን ደምሴ፣ አስፋው ያዕቆብ እና ክልቱ አያኖ ክለቡን በሚመሰርቱበት ወቅት ቤሳ ቤስቲን እንኳ ኪሳቸው ውስጥ ስላልነበራቸው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ተሰብስበው በሰፊው ተወያዩ። በዚህ የውይይት ወቅት ነው ገንዘብ ለማግኘትና የክለቡን መመስረት እውን ለማድረግ የቡሄ ቀን እጅግ መልካምና ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን የተረዱት። ዘጠኙ ወጣቶች በአንድ ድምፅ ተስማምተው በታሪካዊው የቡሄ ዕለት ማለትም ነሐሴ 13 ቀን 1927 ዓ.ም. በጋራ በመሆን ቡሄ ጨፍረው (ሆያ ሆዬ ብለው) በሚያገኙት ማናቸውም ነገር የክለቡን የመጀመሪያ ማሊያ ለመግዛት ቁርጥ የሆነ ውሳኔ ላይ ደረሱ። በዚያን ጊዜ የነበረው የባህል ልማድ አሁን ካለው የተለየ በመሆኑ፣ ቡሄ ሲጨፈር የሚሰጠው ጥሬ ገንዘብ ሳይሆን ሙልሙል ዳቦ ነበር። በመሆኑም ዘጠኙ ተጫዋቾችና መስራቾች ቀደም ሲል ከሚጨፍሩበትና ለምደውት ከነበረው አካባቢ ራቅ ብለው በመንቀሳቀስ በየቤቱ በር እያንኳኩ በደመቀ ሁኔታ ጨፈሩ፤ በዚህም ጥረታቸው በርካታ ቁጥር ያለው የሙልሙል ዳቦ በአንድነት ማሰባሰብ ቻሉ ታሪካዊውን ስራ ሰሩ። ይሁን እንጂ የተሰበሰበውን ይህንን በርካታ ዳቦ ወደ ጥሬ ገንዘብ ለመቀየር አዲስ አበባ ውስጥ ወደሚገኘው ሰራተኛ ሰፈር ለሚገኙ ወዛደሮች ለመሸጥ ዳቦውን በከረጢት ይዘው ጉዟቸውን ጀመሩ። በዚህ የጉዞ መስመር ላይ ሳሉ ግን ያልተጠበቀ ፈተና ገጠማቸው፤ በመንገድ ላይ ያገኟቸው “ዱርዬዎች” ከተሰበሰበው ዳቦ ላይ የተወሰነውን ነጠቋቸው። ወጣቶቹ ተስፋ ሳይቆርጡ ጉዟቸውን በመቀጠል የተረፈውን ዳቦ ለሰራተኛ ሰፈሩ ወዛደሮች በመሸጥ ማሊያ መግዣ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ በእጃቸው አስገቡ። ከዳቦው ሽያጭ የተገኘችው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን በወቅቱ መገበያያ በትክክል ሁለት ጠገራ ብር ነበረች። የክለባችው የመጀመሪያ መለያ ቡናና ነጭ ነበር። ቡናና ነጭ መሊያን የገዙት ግን ፈልገው አልነበረም በቂ ገንዘብ ስላልነበራቸው በሁለት ጠገራ ብር ከፒያሳ «ግሪካዊ አውግስታስ ዱስ» ከተባለ ሱቅ በርካሽ ስላገኙት ነበር። ይህ በቡሄ ዕለት የተጀመረው ታሪካዊ የማሊያ ግዢ በኋላ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በታህሣሥ ወር 1928 ዓ.ም. በይፋ ተመሠረተ። ክለቡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለብ በመሆን ታሪካዊ ማዕረግንና ቀዳሚነትን ተቀዳጀ። በ1928 ዓ.ም. በይፋ የተመሰረተው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በታሪኩ የመጀመሪያውን የሜዳ ጨዋታ ያደረገው ከ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ነበር። በዚሁ ታሪካዊ የመጀመሪያ ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። በዕለቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠንካራ ተፎካካሪ ከነበረው የ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ለመጫወት ወደ ሜዳ ሲያመራ፣ አስቀድመው ከተመረጡትና ቡድኑን ካደራጁት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ባልታወቀ ምክንያት ሳይመጣ ቀረ። በዚህ ድንገተኛ መቅረት ምክንያት ቡድኑ በሰው ጎደሎ ለመጫወት በተገደደበት ወሳኝ ሰዓት፣ መስራቾቹ በሜዳው አቅራቢያ መንገድ ላይ ሲጫወት ያገኙትን አንድ ታዳጊ ወጣት ተመለከቱ። ይህ ታዳጊ በወቅቱ ገና የ14 ዓመት ዕድሜ የነበረውና በኋላ ላይ የኢትዮጵያ ስፖርት ባልደረባ የሆነው ይድነቃቸው ተሰማ ነበር። ወጣቶቹም ያለ ምንም ቅድመ ዝግጅት ቡድኑን እንዲሞላ ድንገት ጋበዙት፤ እርሱም የቀረበለትን ጥሪ በደስታ ተቀብሎ በአጋጣሚ ወደ ሜዳ ገባ። ያለ ምንም ልምምድና ዝግጅት በድንገት የተሰለፈው ይድነቃቸው ተሰማ፣ በሜዳ ላይ ያሳየው አስደናቂ ችሎታና ቅልጥፍና ሁሉንም ያስገረመ ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ታሪካዊ ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ፣ ለክለቡ የመጀመሪያውን ድል ያስገኙትን ሁለቱንም ታሪካዊ የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ይኸው መንገድ ላይ ተገኝቶ በድንገት የተሰለፈው ታዳጊ ይድነቃቸው ነበር። ይህ ብቃት ገና በታዳጊነቱ በክለቡ ውስጥ ያለውን የማይተካ ቦታ ከማረጋገጡም በላይ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን የድል ጉዞ በደመቀ ሁኔታ እንዲጀመር አድርጓል። ቡሄ በዓል እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ያላቸው ታሪካዊ ቁርኝት የክለቡን ጥልቅ ህዝባዊና ባህላዊ መሰረት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቀዳሚ ፋና ወጊ የሆነው ይህ ታላቅ ክለብ፣ በታሪካዊቷ የነሐሴ 13 ቀን የቡሄ ዕለት የመስራቾቹ የ"ሆያ ሆዬ" ጨዋታና ከተሰበሰበው ሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ባገኟት ሁለት ጠገራ ብር የመጀመሪያውን ቡኒና ነጭ ማሊያ መግዛቱ፣ ክለቡ ከህዝብ ማህፀን የወጣ የህዝብ ሀብት መሆኑን ያረጋግጣል። ይህ ከባህልና ከትውፊት ጋር የተቆራኘ አስደናቂ አጀማመር፣ ከጊዜ በኋላ በ1928 ዓ.ም. ለይፋዊ ምስረታው በር ከፋች ከመሆኑም በላይ፣ በታሪካዊው የመጀመሪያ ጨዋታ ላይ እንደ ይድነቃቸው ተሰማ ያሉ የአፍሪካ እግር ኳስ ታላላቅ መሪዎችና ድንቅ ተሰጥኦዎች እንዲፈጠሩ መሰረት የጣለ የኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ነው።
የግብጽ እኩይ ሴራ የማይገታው የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት መብት
Aug 19, 2026 175
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች የምትገኘው እና የቀጣናው የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋት ዋና መሠረት ነች። የኢትዮጵያ፣ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የፖለቲካ ፍላጎት ሳይሆን ሀገራዊ ሕልውናንና ደህንነትን የማረጋገጥ፣ የልማትና ብልጽግናን ዕውን የማድረግ የትውልድ ጥያቄ ነው። ትልቅ አቅም ያላት ኢትዮጵያ በመልክዐ-ምድራዊ እስር ውስጥ እንድትቀር የሚደረገው ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍትሕን የሚቃረን አካሄድን ለማረም ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት የነበራት የባህር በር ባለቤትነት እና የማሪታይም መብት በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እየሰራች ነው። ይህ የኢትዮጵያ ፍትሐዊና የማይቀረው የሕልውና ጥያቄ በዓለም አቀፉ የባሕር ሕግ ኮንቬንሽን (UNCLOS) የተረጋገጠ እና በጋራ ተጠቃሚነት (Win-Win) መርሕ ላይ የተመሠረተ ቢሆንም፣ የግብጽ ፖሊሲ አውጪዎች ግን ይህንን የሕልውና ጥያቄ ለማክሸፍ የሴራ እና የከበባ ስትራቴጂያቸውን ለማስፈጸም እየሰሩ ይገኛሉ። የግብጽ ሴራ በዋናነት ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ለወደብ ኪራይ እንድታወጣ በማስገደድ፣ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት የሚወጣው ካፒታል እንዲሟጠጥ በማድረግ የሀገሪቱን የኢንዱስትሪያላይዜሽንና የልማት ዕድገት ለማቀጨጭ ያለመ የኢኮኖሚ ዘመቻ ነው። በተጨማሪም ግብጽ የቀይ ባሕርን ማሪታይም ቀጣና “የባሕር ዳርቻ ሀገራት ብቻ (Littoral States) ይዞታ" አድርጋ በመሳል፣ የኢትዮጵያን ታሪካዊና ሕጋዊ የመጠቀም መብት በመካድ ከማንኛውም የቀይ ባሕር የደህንነትና የኢኮኖሚ ስብስብ እንድትገለል እየሰራች ትገኛለች። ግብጽ ከኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርጋቸው ወታደራዊ ስምምነቶች በሰሜንና በምሥራቅ ድንበሮች አካባቢ አዲስ የደህንነት ስጋት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ ሀብቷንና ትኩረቷን ወደ የብስ ጥበቃ እንድታዞርና ለባህር ኃይል ግንባታ የምታውለውን አቅም እንድታበታትን የታለመ የከበባ ስልትም ነው። በዓለም አቀፍ የፋይናንስና የኢንቨስትመንት ተቋማት ዘንድ የምታደርገው የዲፕሎማሲ ጫና፣ ኢትዮጵያ ለወደብ እና ለትራንስፖርት ኮሪደሮች ልማት የሚሆን የውጭ ኢንቨስትመንት እንዳታገኝ እና የቀይ ባሕር አካባቢ የስጋት ቀጠና ተደርጎ እንዲቆጠር በማድረግ ኢንቨስተሮች እንዲሸሹ በማድረግ ላይ ናት። በጎረቤት ሀገራት ዘንድ የጥርጣሬ እና የስጋት ግንብ በመገንባት፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር የምታደርጋቸው ፍትሐዊና የጋራ ዕድገትን ያለሙ የወደብ ስምምነቶች የሉዓላዊነት መጣስ ተደርገው እንዲቆጠሩ የማስፈራራትና የሐሰት ትረካና ዘመቻ ታካሂዳለች። ግብጽ የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት ላይ አንድ ወጥ አቋም እንዳይዙ ለማድረግ ድርጅቶቹን የፖለቲካ ፍልሚያ መድረክ በማድረግ የቀጣናውን ተቋማዊ ትብብር የማደናቀፍ ተግባር እያከናወነች ይገኛል። የግብጽ ሚዲያዎች የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ የ130 ሚሊዮን ሕዝብ የረጅም ጊዜ ሕልውና እና የትውልድ ጥያቄ መሆኑ እየታወቀ ጠባብ የፖለቲካ አጀንዳ በማስመሰል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲይዝ የማድረግ ስራ ላይ ተጠምደዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና (AfCFTA) ውስጥ የምታደርገውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ፣ የወደብ ትራንዚት ወጪዋ ከፍተኛ ሆኖ እንዲቀጥል በማድረግ ምርቶቿ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ጫና ለመፍጠር ትሰራለች። የግብጽ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን ለዘለቄታው የመልክዐ-ምድር እስረኛ አድርጎ በማስቀረት፣ በምሥራቅ አፍሪካ የሚኖራትን ጂኦ-ፖለቲካዊና የኢኮኖሚ የበላይነት መግታት ነው። ሆኖም የግብጽ ሴራ የኢትዮጵያን የልማት መንገድ ሊያስቆመው አይችልም። ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በሕዝቦቿ የማይበገር ጽናትና ቁርጠኝነት እውን እንደሆነ ሁሉ፤ በቀይ ባህር ላይ ህጋዊና ፍትሃዊ መብትን የማረጋገጥ ጉዞም የቀጣናውን የታሪክ ሂደት የሚቀይር የማይቀለበስ ብሔራዊ የህልውና ጉዳይ ነው።
ቡሄ የትውልድ ወጋገን፤ የማኅበራዊ ትስስር አምድ
Aug 19, 2026 103
ቡሄ በወርሃ ነሐሴ በ13ኛው ቀን ህፃናት ሆያ…. ሆዬ….! ሆ…. በሚል ዜማና ጅራፍ እያጮሁ የሚያከብሩት፤ እናቶች ለህፃናቱ ሙል ሙል ዳቦ በመስጠት እንኳን አደረሳችሁ እያሉ በድምቀት የሚያከብሩት በዓል ነው። ቡሄ ትርጓሜውም ብርሃን፣ብራ፣ ወጋግን ማለት ሲሆን ከጨለማ ወደ ብርሃን የመሸጋገሪያ የተስፋ ምልክት ነው። በሀይማኖታዊ አንድምታው በዓሉ የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ ብርሃን በደብረ ታቦር ተራራ ላይ መገለጡ የሚታሰብበት ነው፤ በዚህም ደብረ ታቦር ይባላል፡፡ የክረምቱ ጭጋግ ተገፎ የብርሃን ወጋገን የሚታይበት ሕፃናትና ወጣቶች በየቤቱ እየዞሩ «ሆያ ሆዬ» በማለት በረከትና ምርቃት የሚያፍሱበት የደስታና የፍቅር መግለጫ ነው። ህፃናትና ወጣቶች በየዕድሜያቸው ጅራፍ እያጮሁ በሕብረ ዝማሬዎች እየደመቁ በአብሮነት እና በደስታ የሚያከብሩት ትውፊታዊ በዓል ነው ቡሄ። የወጣቶችን ጉርብትና እና ማኅበራዊ ትስስር የሚያጎለብት እሴት ነው፤ በአከባበሩ ወቅት የሚንጸባረቀው የመረዳዳትና ያለውን የመካፈል ባህል ፋይዳውን ከትውልድ ወደ ትውልድ ማሸጋገር ያስችላል። የቡሄ በዓል ባህላዊ እሴቶችን በመጠበቅ፣ ትውልድን በማቀራረብ እና ማኅበራዊ ትስስርን ይበልጥ በሚያጠናክር ተምሳሌትነቱ እልፍ ነው። በአዲስ አበባ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከፍተኛ የቅርስ ጥናት ተመራማሪ መምህር መክብብ ገብረማሪያም ለኢዜአ እንዳሉት፤ የቡሄ በዓል የብርሃን ዘመን መምጣቱን የተስፋ ጎህ መቅደዱን ማብሰሪያ ነው፡፡ ቡሄ ከጨለማ ወደ ብርሃን ሽግግር መምጣቱን የሚያበስር በታዳጊዎች የሚዘከር የፍቅር፣ የአንድነትና የበረከት መገለጫና ተስፋ መሆኑን ያነሳሉ፡፡ ታዳጊዎችና ወጣቶች በበዓሉ ወቅት የሚያዜሙት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሸጋገር የመጣው የ«ሆያ ሆዬ» ሕብረ ዜማ ለጋራ ትርክት ግንባታ ገንቢ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል። ቡሄ የትውልድ ወጋገን፤ የማኅበራዊ ትስስር አምድ በመሆኑ ማኅበራዊ ትስስርና የጋራ ዕሴቶችን ማጠናከር ያስችላል ብለዋል።   ታዳጊው በሱፈቃድ አስሜ ቡሄ ከጓደኞቹ እና ከወዳጅ ዘመዶቹ ጋር ፍቅርንና አብሮነትን ይበልጥ የሚያጠናክርበት የደስታና የተስፋ በዓል መሆኑን ይናገራል፡፡ ቡሄ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠብቀውና ቀጣይ ሕይወቱን በአዲስ መንፈስ ለመምራት አቅም የሚፈጥርለት የብሩህ ዘመናትን ማለሚያ መሆኑን ይገልፃል። ቡሄ ከታላላቆቹ የወረሰው ከእኩዮቹ ጋር በፍቅርና በደስታ የሚያከብረው ነገን በተስፋ የሚያይበት ውብ በዓል እንደሆነ የሚናገረው ደግሞ ታዳጊው በረከት ምናለ ነው፡፡   የተጣሉ ጓደኛሞች እርቅ የሚያወርዱበት በዓል በመሆኑ ለትውልድ አንድነት እና አብሮነትን በማስተማር ረገድ ትልቅ ድርሻ አለውም ብሏል። ወጣት ያብስራ ጸጋዬ በበኩሉ ቡሄ በዓመት አንድ ጊዜ የሚመጣ፤ ተራርቀው ከሚኖሩ የተለያዩ አካባቢ እኩዮቹ ጋር በአንድነት የሚያከብሩት በዓል መሆኑን ይናገራል፡፡   ከሁሉም ዓይነት ሕብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ታዳጊዎች የሚሰባሰቡበት፤ ሕብረ ብሔራዊነትን የሚያጠናክር የጋራ በዓል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ በኃይሉ ሞገስ ናቸው።      
የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ ነው
Aug 19, 2026 116
ወላይታ ሶዶ ፤ ነሐሴ 13/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አስቴር ዳዊት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ ትግበራ በስኬትና በውጤታማነት ተጠናክሮ መቀጠሉ ይታወቃል።   የዲጂታል መሠረተ ልማቶች መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሳይበር ጥቃቶችን የመከላከልና የሳይበር ሉዓላዊነትን የማስከበር ተግባርም በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል። ይህንኑ ተግባራዊ ጥረት ለማጠናከርም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ከተለያዩ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የወጣቶችን የሳይበር ደህንነት ክህሎት የሚያሳድጉ የክረምት ስልጠና ፕሮግራሞችን በማካሄድ ላይ ይገኛል።   በተለይም የክረምት የስልጠና መርሃ-ግብር በሳይበር ደህንነት፣ በሶፍትዌር ልማት፣ በኮዲንግ እና በመረጃ ደህንነት ዙሪያ የተሻለ ክህሎት ያላቸውን ታዳጊና ወጣቶች በመሰልጠን ላይ ናቸው። በዚሁ መሰረትም የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በክረምቱ በአምስተኛ ዙር በርካታ ወጣቶችን የሳይበር ደህንነት ስልጠና በመስጠት ላይ ሲሆን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አስቴር ዳዊትና ሌሎች የመንግስት ስራ ኃላፊዎች በስፍራው በመገኘት ሰልጣኞችን አበረታትተዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የወጣቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን አንስተው በዚሁ መሰረትም የስልጠና እና ግንዛቤ ስራዎች መቀጠላቸውን ገልጸዋል። በክረምቱ ወላይታ ሶዶን ጨምሮ በስድስት ዩኒቨርሲቲዎች ለወጣቶች ተመሳሳይ ስልጠና በመሰጠት ላይ መሆኑን አንስተው ይህም ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም የሚሆን ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን አንስተው ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል።   የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳይ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት አክበር ጩፎ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ብቁ ዜጎችን የማፍራት ስራውን መቀጠሉን ገልጸዋል። ከቴክኖሎጂ፣ ከኢንዳስትሪና መሰል ተቋማት ጋር የመስራት ዕድል መፈጠሩን ጠቁመው ይህም የተለየ ተሰጥኦ ላላቸው ተማሪዎች መልካም እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።   ከሰልጣኞቹ መካከል ከዲላ ከተማ የመጣችው የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው መልካም አስራት እና ከሐዋሳ ከተማ የመጣችው የ11ኛ ክፍል ተማሪ ኖሐሚን ንጋቱ፤ በስልጠናው ስለ የሳይበር ደህንነትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ መሰረታዊ ዕውቀት በመገብየት በዲጂታሉ ዓለም የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረን አድርጎናል ብለዋል። የወላይታ ሶዶ ነዋሪና በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ ዓመት ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ፍሬው ቶማስ በበኩሉ ይህ ስልጠና ክህሎታቸውን ለማሳደግ አማራጭ ላጡ ወጣቶችና ተማሪዎች መልካም ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል።   በስልጠናው የሳይበር ደህንነት እውቀት ማግኘቱን የጠቀሰው ወጣቱ የመረጃ መንታፊዎችን በመዋጋት የሀገራችንን የመረጃ ደህንነት ለማረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ አረጋግጧል ።
የሚታይ
ፌዴራል ፖሊስ የፀጥታ ስጋቶችን በላቀ ብቃት ለመመከት ዝግጁ ነው - ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል
Aug 19, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የፀጥታ ስጋቶችን በላቀ ብቃት በማክሸፍ የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገለጹ፡፡ የፌደራል ፖሊስ ስትራቴጂክ አመራሮችና ከፍተኛ የፖሊስ መኮንኖች በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፀጥታ እቅድ ዙሪያ መክረዋል፡፡   ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በዚህ ወቅት ተቋማቸው የሠራዊቱን ሥነ ልቦና በመገንባት፣ የወትሮ ዝግጁነት በማጠናከርና የማድረግ አቅሙን ይበልጥ በማሳደግ ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን የመጠበቅ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ እድገት እያሳየች ባለችበት ወቅት ሰላሟንና እድገቷን የማይፈልጉ አካላት የደቀኑትን የፀጥታ ስጋት ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍለን ለማክሸፍ ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡   በመድረኩ በሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ እና በወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ የመወያያ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት መሆኑንም የፌደራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡
መደመር የደረመሠው የጠላት ካምፕና የባንዳዎች እሪታ
Aug 19, 2026 304
በምስራቅ አፍሪካና በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የካይሮ እጅ ሁልጊዜም ኢትዮጵያን ማዕከል ያደረጉ እኩይ ስትራቴጂዎችን በመተለም ይታወቃል። የዓባይ ወንዝ ዋነኛ ምንጭና የተፈጥሮ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያን ማዳከም፣ የውስጥ ግጭቶችን ማበረታት እና በቀይ ባሕር እንዲሁም በኤደን ባሕረ-ሰላጤ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍላጎት ማደናቀፍ የግብፅ የረጅም ጊዜ የውጭ ፖሊሲ መሠረት ሆኖ ቆይቷል። ግብፅ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በወታደራዊ ኃይል ኢትዮጵያን በግልጽ ወርራ ለመቆጣጠር ባደረገችው ሙከራ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1875 በጉንደት እንዲሁም 1876 በጉራዕ ጦርነቶች በኢትዮጵያ አሳፋሪ ሽንፈት አስተናግዳለች ። ከዚህ የቀጥታ ወታደራዊ ሽንፈት በኋላ ካይሮ ኢትዮጵያን በግልጽ ጦርነት ማንበርከክ እንደማትችል ተረድታ ወደ ተዘዋዋሪ የውስጥ ሴራና የእጅ-አዙር ጦርነት ተሸጋግራለች። ካይሮ ኢትዮጵያ ጠንካራና የበለፀገች ሀገር ሆና ከተነሳች በዓባይ ውሃ ላይ ያላትን አጠቃላይ የበላይነት እንደምታጣ ስለሚሰማት፣ የሀገሪቱን እድገት የማደናቀፍና በጂኦፖለቲካው መስክ ወደብ አልባ አድርጎ የመዝጋት ስትራቴጂን ለዘመናት ስትከተል ኖራለች። ይህም የታሪክ እውነታ ከትላንት እስከ ዛሬ በስውርና በግልጽ የሴራ መረቦች ተሸርቦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሲፈታተን የኖረ መራራ እውነት ነው። የቡትሮስ ብትሮስ ጋሊ የዲፕሎማሲ ሽፋን እና ኢትዮጵያን ወደብ የማሳጣት ሴራ በታሪክ አጋጣሚዎች እንደምናየው፣ በግብፅ የፖለቲካ ልሂቃን የታቀዱ ሴራዎች በዓለም አቀፍ መድረኮች እንዴት ተግባራዊ እንደሆኑ አንደኛው ማሳያ የቀድሞው ግብፃዊ ዲፕሎማት ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ አካሄድ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በ1970ዎቹ መጨረሻ በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራር በነበሩበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ በውስጥ ግጭት እንድትታመስና የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ ስጋት እንዳትሆን ከበስተጀርባ የዓመፅ ኃይሎችን የማጠናከር ስራ ሲሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ሃቅ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በውሃ ፖለቲካ ረገድ በሰጡት የታወቀ ንግግራቸው “ቀጣዩ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና የሚካሄደው ጦርነት በፖለቲካ ምክንያት ሳይሆን በውሃ ምክንያት የሚደረግ ይሆናል” በማለት ለቀጣናው ያሰቡ መስለው የካይሮን የውሃ የበላይነት ስጋትና ፍላጎት በግልጽ አንጸባርቀው ነበር። ይህ ንግግራቸው ግብፅ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት የመቆጣጠር ፍላጎቷንና ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ የልማት ፕሮጀክቶችን እንዳታካሂድ ለማድረግ የምታደርገው ሴራ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲያገኝ ዓላማ ያደረገ አደገኛ ንግግር ነው። በኋላም እ.ኤ.አ በ1993 ኤርትራን ከኢትዮጵያ በመገንጠል ሂደት ውስጥ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የስድስተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ ነበሩ። በወቅቱ 99 ነጥብ 8% የሚሆኑት ኤርትራዊያን በሕዝበ ውሳኔ ነጻ ሀገርንትን መርጠዋል በሚል ሕወሃትና ሻዕቢያ የሰሩት ድራማ ተቀባይነት አንዲያገኝ የተመድ ዋና ጸሐፊው ከፍተኛ ሴራ ሰርተዋል። ይህ የኤርትራ ህዝብን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በሻዕቢያ ባርነትና ግዞት እንዲማቅቅ ያደረገው የሕዝበ ውሳኔ ድራማ ላይ ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊ የመሪ ተዋናይነትን ሚና ተጫውተዋል። በሂደቱም ዋነኛ ዓላማቸው የሆነውን ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በሯን እንድታጣ አድርገዋል። ይህም የካይሮ የረጅም ጊዜ “ኢትዮጵያን የመዝጋት” ስትራቴጂ አካል እንደነበር ግልጽ ነው። የካይሮ መጥረቢያ እና አሁናዊው የጥፋት መንገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት የመጥረቢያ ተምሳሌታዊ ማብራሪያ፣ ሕገ ወጡ ሕወሃትን እንደ መጥረቢያ ብረት፤ ሻዕቢያን ደግሞ እንደ መጥረቢያ ዛቢያ ያስቀመጡ ሲሆን፤ መጥረቢያውን የሚያዘውና የሚወረውረው ሌላ ሶስተኛ አካል መኖሩንም ተናግረዋል። እንደሚታወቀው መጥረቢያ አንድን ነገር የመቁረጥና የማፍረስ ስራ ለማከናወን የሶስት አካላት ቅንጅት ያስፈልገዋል፦ ወርዋሪው (እጁ)፣ ዛቢያው (መያዣው) እና ብረቱ (ቁራጩ)። በዚህ ተምሳሌት ውስጥ ወርዋሪው ወይም መጥረቢያውን ጨብጦ ስራ ላይ የሚያውለው አካል ግብፅ ናት። ወርዋሪው ሁልጊዜም ከበስተጀርባ ሆኖ ስትራቴጂ ይነድፋል፣ ፋይናንስና ወታደራዊ ድጋፍ ያቀርባል፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሽፋን ይሰጣል። በሌላ በኩል የመጥረቢያ ብረት ያለ ዛቢያው (መያዣው) ኃይል አግኝቶ ማረፍ አይችልም፤ ዛቢያውም ያለ ወርዋሪው እጅ መንቀሳቀስ አይችልም። በዚህ ሂደት ሻዕቢያ (እንደ ዛቢያ) በቀጣናው ውስጥ የካይሮን ፍላጎት ለማስፈጸም የመያዣነት ሚና ይጫወታል። ቀጣናውን ለማተራመስ በሞመከር የካይሮን ስትራቴጂካዊ ፍላጎት ለማሳካት መንገድ ይከፍታል። ህገ-ወጡ ህወሓት ደግሞ እንደ መጥረቢያ ብረት በሀገር ውስጥ ሆኖ የሀገሪቱን መዋቅር፣ የህዝቦችን አንድነት እና ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ጥቅም ለመሸርሸር የሚሰራ ተላላኪ መሳሪያ ነው። በዚህ የሴራ ትስስር አሁን ላይ ኢትዮጵያ በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት ማደናቀፍ ዋነኛ ዓላማው አድርጎም እየሰራ ይገኛል። ግብፅ “የቀይ ባሕርና የኤደን ባሕረ-ሰላጤ የባሕር ወሰን ያላቸው ሀገራት ብቻ ናቸው በውሃው ላይ መወሰን ያለባቸው” የሚል መርህ በማንሳት፣ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትንና በቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኘውን ትልቁን ኢኮኖሚ (ኢትዮጵያን) ያገለለ ህገ-ወጥ ስብስብ ለመፍጠር እየሰራች ነው። በተጨማሪም በቅርቡ ከሶማሊያና ከሌሎች የአካባቢው ሀገራት ጋር የተደረጉ የውትድርናና የደህንነት ስምምነቶች፣ የሶማሊያን ሰላም ለማስጠበቅ ሳይሆን ቀጣናውን ለማተራመስና ወታደራዊ ስጋት ለመፍጠር የተቃኙ ናቸው። ይህ ሁሉ አካሄድ ዋነኛ ዓላማው ቀጣናውን የውክልና ጦርነት ማዕከል በማድረግና ኢትዮጵያ ወደ ባሕር እንዳትቀርብ ሆነ ተብሎ የተሰላ ሴራ ነው። ከቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ እስከ ዛሬው የቀይ ባሕር ሴራዎች ድረስ የተዘረጉት መረቦችም ይህንኑ እውነት ያሳያሉ። የካይሮ መጥረቢያዎችን ያዶለዶመው የመደመር መንግሥት ጥንካሬ ግብጽ እያከናወነችው ባለው አሁናዊ ሴራ ውስጥ የካይሮ ስትራቴጂስቶች የሳቱት ትልቅ እውነታ አለ። የግብጽ የሴራ መጥረቢያዎች ለመቁረጥ የሚሞክሩት በፈተናዎች የማትበገረውን እና እንደ ወርቅ በእሳት ውስጥ ተፈትና ያለፈችውን ኢትዮጵያን መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በታሪኳ የውጭ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎችን አሸንፎ መውጣት እንግዳ የሆነባት ሀገር አይደለችም። ባለፉት ክፍለ ዘመናት በወረራ፣ በውስጥ አለመረጋጋትና በጂኦፖለቲካዊ ከበባዎች ውስጥ አልፋ የጸናች ሀገር ናት። ወርቅ በእሳት ውስጥ ሲያልፍ ቆሻሻው ተወግዶ ይበልጥ እንደሚበራ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በተጋረጡባት የህልውና ፈተናዎች ሁሉ አልፋ ይበልጥ እየጠነከረችና እየተደራጀች መምጣቷ የታሪክ እውነታ ነው። አሁን ባለንበት ዘመን ደግሞ ይህ ጥንካሬዋ ይበልጥ ጎልብቷል። የመደመር መንግሥት ቁልፍ ፍልስፍና እና እየተገበራቸው ያሉ እርምጃዎች የካይሮን የረጅም ጊዜ የእጅ አዙር ጦርነትና ሴራዎችን ከንቱ ያደረገ ነው። የመደመር መንግሥት የውጭ ጫናዎችንና ሴራዎችን ለመመከት የመጀመሪያው ምሽግ የውስጥ አቅምን ማጠናከር መሆኑን በመገንዘብ፣ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለፍፃሜ ማብቃትና ግዙፍ የግብርና፣ የአረንጓዴ አሻራ እና የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን እውን አድርጓል። ይህም ግብፅ ኢትዮጵያን በልማት እንዳትበለፅግ ለማድረግ ያቀደችውን ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ አክሽፎታል። ካይሮ ኢትዮጵያን በጂኦፖለቲካዊ ከበባ ለማዳከምና በውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የነደፈችው የረጅም ጊዜ የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት ባስመዘገባቸው የልማትና የዲፕሎማሲ ድሎች ምክንያት ሙሉ በሙሉ ተደርምሷል። ይህ የጠላት ካምፕ መደርመስና የኪሳራ ስሌት ደግሞ በካይሮ ስትራቴጂስቶችና በውስጥ ተላላኪዎቻቸው (ባንዳዎች) ዘንድ ታላቅ ድንጋጤንና ተስፋ የመቁረጥ እሪታን ፈጥሯል። በመሆኑም የተበተነው የጠላት ካምፕና የተበሳጩት ባንዳዎች ብቸኛ አማራጭ አድርገው የያዙት በሳይበርና በሚዲያ ምህዳር የሃሰት መረጃዎችን ማንደድና የፕሮፓጋንዳ ማዕበል መፍጠር ቢሆንም፣ ይህም የተስፋ መቁረጥ ድምፅ ብክለት እንጂ የኢትዮጵያን የጽናት ጉዞ የሚያስተጓጉል አይሆንም። በሌላ በኩል ግብፅ “የቀይ ባሕር ሀገራት ጥምረት” በሚል ስም ቀጣናውን ለማተራመስና እርስ በርስ ጥርጣሬ ለመፍጠር የምታደርገውን የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት የጋራ እድገትና የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በማስቀደም በዲፕሎማሲው መስክ እየመከተው ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ምክክር የጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ በጋራ እንዲወስኑ በማድርግም የካይሮ ስትራቴጂስቶች በኢትዮጵያ የውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የጠነሰሱትን ሴራ ከንቱ አድርጎታል። በአጠቃላይ ታሪክ እንደሚነግረንና የወቅቱ እውነታ እንደሚመሰክረው፣ የግብፅ የሴራ መጥረቢያዎች በፈተናዎች እሳት ተፈትና ባላለፈች ደካማ ሀገር ላይ ያረፉ አይደሉም። ለመቁረጥ የሞከሩት በጽናት፣ በህዝቦቿ መስዋዕትነትና በፅኑ ታሪካዊ መሰረት ላይ የቆመችውን ኢትዮጵያን ነው። አሁን ላይ በመደመር መንግሥት መሪነት እየተገነባ ያለው የውስጥ አቅም፣ የልማት ስኬትና በራስ መተማመን የካይሮን የረጅም ጊዜ የከበባ ሴራ ሙሉ በሙሉ ወድቅ ማድረጉን ቀጥሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ሁሉ አሸንፎ ማለፍ የሰርክ ተግባሯ እንደመሆኑ መጠን፣ የዛሬውንም የጂኦፖለቲካ ውጥረትና የሴራ መረብ በጽናት አልፋ የቀጣናው የልማትና የሰላም ማዕከል ሆና መቀጠሏ የማይቀየር እውነት ነው።
ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት ኖርዌይ ትደግፋለች
Aug 19, 2026 163
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ ኖርዌይ ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትደግፍ በኢትዮጵያ የኖርዌይ ኤምባሲ የደንና አየር ንብረት ጉዳዮች ልዩ መልዕክተኛና አማካሪ ላይቭ ጃኮብ ሲድነስ ገለጹ። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ስጋት የሆነውን የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ለመከላከል በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ በአረንጓዴ ልማትና በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ለቀጣናው ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ተግባር በማከናወን ላይ ትገኛለች። በኢትዮጵያ የኖርዌይ ኤምባሲ የደንና አየር ንብረት ጉዳዮች ልዩ መልዕክተኛና አማካሪ ላይቭ ጃኮብ ሲድነስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በደን ልማት ዘርፍ አስደናቂ ለውጥ ተገኝቷል፡፡   በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርና በአፈርና ውሃ ጥበቃ በተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በሀገሪቱ የደን ሽፋን ላይ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ ኖርዌይ ባለፉት አስርት ዓመታት ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የደን ሽፋን ማሳደግ የሚያስችል እንቅስቃሴ አድርገናል ብለዋል፡፡ የደን ልማት የአፈር መሸርሸርን መከላከልና የአፈርና ውሃ ሀብት ጥበቃ በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንደሚያሳድግ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የደን ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ በቀጣናው የውኃ አቅርቦትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እገዛ እንደሚያደርግም ተናግረዋል፡፡ ኖርዌይ ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትደግፍም ገልጸዋል። ሁለቱ ሀገራት በደን ጥበቃ ስራዎች በመተባበር የደን ጭፍጨፋን ለመቀነስ እንደሚሰሩ ጠቅሰው፤ ኖርዌይ የኢትዮጵያ የሬድ ፕላስ መርሃ ግብር ትግበራ ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኗን ተናግረዋል።   በኢትዮጵያ የተነደፈውን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የሚቋቋም አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ለመደገፍ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥልም ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ ምርቶቿን በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ የወጪ ንግድ አቅሟን እያሳደገች ነው
Aug 19, 2026 173
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ምርቶቿን በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ የወጪ ንግድ አቅሟን እያሳደገች መሆኑን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ከሚገኘው የቻይና ኤምባሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢትዮጵያና የቻይናን ዘላቂና ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ወደ ላቀ የንግድና ኢኮኖሚ ትስስር የሚያሸጋግረውና የፕሮሞሽን ሥራዎች አካል የሆነ "Export to China" መድረክ በይፋ ተጀምሯል።   በመድረኩ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ፣ የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ አስመጪና ላኪዎች ታድመዋል። በመድረኩ የቻይና አስመጪዎች ጥራት ያላቸውን የኢትዮጵያ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በስፋት እንዲገዙ ለማድረግ የሚያስችል የፕሮሞሽን ሥራዎች ተከናውኗል። በዚህም ከ340 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው 33 የንግድ ለንግድ (B2B) የግብይት ኮንትራቶች በቡና፣ ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ በጨርቃጨርቅ እና በማዕድን ዘርፎች ወደ ውጭ ለመላክ ተፈራርመዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት የስምምነቱ ዓላማ የኢትዮጵያን የወጪ ንግድ ገቢ ግኝት ለማሳደግ የሚያስችል የፕሮሞሽን ሥራዎችን በቻይና ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ ከቻይና ኤምባሲ ጋር ሰፋፊ ውይይቶችን ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው፤ ስምምነቱ ከብዙ ሥራዎች በኋላ የተገኘ ውጤት መሆኑንም ገልጸዋል። 33 የሚጠጉ ስምምነቶች መፈረማቸውን ገልጸው፤ እነኝህም 340 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ሊያስገኙ የሚችሉ መሆኑን ጠቁመዋል። ስምምነቱን ወደ ትልቁ የቻይና ገበያ ለመግባት በቻይና መንግሥት የተቀረጸው ኢኒሼቲቭ አካል መሆኑን አንስተዋል። በቡና፣ በቅባት እህል፣ በጥራጥሬ፣ በቆዳ፣ በማዕድን ምርቶች እና በጨርቃ ጨርቅ ላይ ከስምምነት መደረሱን ተናግረዋል። ስምምነቱ ከቃል በዘለለ ተግባራዊ ውጤት የተገኘበት ስኬት መሆኑንም ገልጸዋል። መንግሥት በ2019 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ 13 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ማቀዱን ገልጸው፤ ስምምነቱ ይህንን ማሳካት የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ ምርቶች በዓለም ገበያ የሚያስተዋውቅና ተወዳዳሪነታቸውን በማሳደግ የተያዘውን ውጥን የሚያሳካ መሆኑን አመላክተዋል። በቀጣዮቹ ጊዜያትም ከተለያዩ ሀገራት ጋር ምርቶችን በጥራት በዋጋ እና በብዛት ተወዳዳሪ ሆነው እንዲቀርቡ በትኩረት እንደሚሠራ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጠሉም እንዲሁ።   በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ በበኩላቸው የስምምነቱ ዓላማ ለሁሉም የወጪ ንግድ ትልቅ ገበያ ማግኘት መሆኑን ገልጸዋል። ቻይና በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ እንደምትገኝ ገልጸው፤ የኢትዮጵያ እጅግ አያሌ ምርቶችና የበለጸጉ ተፈጥሯዊ ሀብቶችም እንዲሁ በፍጥነት በማደግ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በሁለቱ ገበያዎች እና ምርቶች መካከል ያለው ትስስር የሀገራቱን እድገት ለማፋጠን አስፈላጊ መሆናቸውንም አመላክተዋል። ስምምነቱ ቻይና ከአፍሪካ እና ከኢትዮጵያ ጋር የዜሮ ታሪፍ ፖሊሲ ከተቀበለች እና መተግበር ከጀመረች ወዲህ የተወሰደ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምክክሩ ኢትዮጵያን ማጽናት የሚያስችል ትልቅ መሰረት እየጣለ ይገኛል-ተመካካሪዎች
Aug 19, 2026 152
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ) ፦ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያን በጠንካራ የተግባቦት ዓለት ላይ ለማጽናት ትልቅ መሰረት እየጣለ እንደሚገኝ ተመካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ለዘመናት በኢትዮጵያ የዘለቁ አለመግባባቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት፣ኢትዮጵያዊያን ካለፈው ኋላቀር እሳቤ በመላቀቅ ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እያደረጉ ይገኛል። ይህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 4 ሺህ ኢትዮጵያውያን እየተመካከሩበት በሚገኘው በዚህ ጉባኤ፣የተመካካሪዎች ሀሳብ በነጻነት የሚንሸራሸርበት ነጻ እና ዴሞክራሲያዊ አውድ ተፈጥሯል። በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሄደ ያለው ይህ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያን በጠንካራ የተግባቦት ዓለት ላይ ለማጽናት ትልቅ መሰረት የሚጥል መሆኑን ከፖለቲካ ፓርቲዎች የተወከሉ ተመካካሪዎች ለኢዜአ ገልጸዋል። ከተመካካሪዎች መካከል የአፋር ነጻ አውጪ ግንባርን ወክለው የመጡት ሀጂ እስማኤል መሀመድ እንዳሉት፣የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በማካተት በሰለጠነ አግባብ እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ ተመካካሪዎች ሃሳባቸውን በነጻነት የሚያንሸራሽሩበት በመሆኑ ዘላቂ ሰላም እና ሀገራዊ መግባባትን ለማስፈን ትልቅ ዕድል እየፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተወክለው የሚወያዩበት ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ የሀገሪቱን የልማት እና የዴሞክራሲ ጉዞ ለማቀላጠፍም ወሳኝ ምዕራፍ እንደሚከፍት ተናግረዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ የሲዳማ አርነት ንቅናቄን ወክለው በመሳተፍ ላይ ያሉት ደምሴ ስኳሬ ፣ የምክክር ሂደቱ ከመነሻው ጀምሮ ግልጽነትና አሳታፊነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሂደቱ ከታች ጀምሮ የተለያዩ ሀሳቦችን በማብሰልና በማዋሃድ ወደ ላቀ የጋራ ሀገራዊ መግባባት የሚያደርስ እና ይህም የሂደቱን የሰለጠነ አካሄድ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ምክክሩ ለሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የመላው ተመካካሪዎች ድምፅ በነጻነት የተደመጠበት ሁሉን አቀፍ ጉባኤ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን በመወከል በመሳተፍ ላይ ያሉት ተመካካሪ ነጻነት ጣሰው ናቸው።   ተመካካሪዎች እርስ በርሳቸው እንዲተዋወቁና ጠንካራ አዎንታዊ ግንኙነት እንዲፈጥሩ ሰፊ ዕድል በመፍጠር ሂደት ውስጥ ልዩ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግረዋል። መድረኩ ኢትዮጵያን የሚያሻግሩ ገንቢ ሀሳቦች እየተነሱበት በመሆኑ የመደማመጥ እና የጋራ መግባባት ባህልን ለማጠናከር ትልቅ አጋጣሚ መፈጠሩንም አንስተዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች መካተታቸው የተሻለች ሀገር በጋራ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የግብጽ እኩይ ሴራ የማይገታው የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት መብት
Aug 19, 2026 175
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች የምትገኘው እና የቀጣናው የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋት ዋና መሠረት ነች። የኢትዮጵያ፣ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የፖለቲካ ፍላጎት ሳይሆን ሀገራዊ ሕልውናንና ደህንነትን የማረጋገጥ፣ የልማትና ብልጽግናን ዕውን የማድረግ የትውልድ ጥያቄ ነው። ትልቅ አቅም ያላት ኢትዮጵያ በመልክዐ-ምድራዊ እስር ውስጥ እንድትቀር የሚደረገው ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍትሕን የሚቃረን አካሄድን ለማረም ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት የነበራት የባህር በር ባለቤትነት እና የማሪታይም መብት በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እየሰራች ነው። ይህ የኢትዮጵያ ፍትሐዊና የማይቀረው የሕልውና ጥያቄ በዓለም አቀፉ የባሕር ሕግ ኮንቬንሽን (UNCLOS) የተረጋገጠ እና በጋራ ተጠቃሚነት (Win-Win) መርሕ ላይ የተመሠረተ ቢሆንም፣ የግብጽ ፖሊሲ አውጪዎች ግን ይህንን የሕልውና ጥያቄ ለማክሸፍ የሴራ እና የከበባ ስትራቴጂያቸውን ለማስፈጸም እየሰሩ ይገኛሉ። የግብጽ ሴራ በዋናነት ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ለወደብ ኪራይ እንድታወጣ በማስገደድ፣ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት የሚወጣው ካፒታል እንዲሟጠጥ በማድረግ የሀገሪቱን የኢንዱስትሪያላይዜሽንና የልማት ዕድገት ለማቀጨጭ ያለመ የኢኮኖሚ ዘመቻ ነው። በተጨማሪም ግብጽ የቀይ ባሕርን ማሪታይም ቀጣና “የባሕር ዳርቻ ሀገራት ብቻ (Littoral States) ይዞታ" አድርጋ በመሳል፣ የኢትዮጵያን ታሪካዊና ሕጋዊ የመጠቀም መብት በመካድ ከማንኛውም የቀይ ባሕር የደህንነትና የኢኮኖሚ ስብስብ እንድትገለል እየሰራች ትገኛለች። ግብጽ ከኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርጋቸው ወታደራዊ ስምምነቶች በሰሜንና በምሥራቅ ድንበሮች አካባቢ አዲስ የደህንነት ስጋት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ ሀብቷንና ትኩረቷን ወደ የብስ ጥበቃ እንድታዞርና ለባህር ኃይል ግንባታ የምታውለውን አቅም እንድታበታትን የታለመ የከበባ ስልትም ነው። በዓለም አቀፍ የፋይናንስና የኢንቨስትመንት ተቋማት ዘንድ የምታደርገው የዲፕሎማሲ ጫና፣ ኢትዮጵያ ለወደብ እና ለትራንስፖርት ኮሪደሮች ልማት የሚሆን የውጭ ኢንቨስትመንት እንዳታገኝ እና የቀይ ባሕር አካባቢ የስጋት ቀጠና ተደርጎ እንዲቆጠር በማድረግ ኢንቨስተሮች እንዲሸሹ በማድረግ ላይ ናት። በጎረቤት ሀገራት ዘንድ የጥርጣሬ እና የስጋት ግንብ በመገንባት፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር የምታደርጋቸው ፍትሐዊና የጋራ ዕድገትን ያለሙ የወደብ ስምምነቶች የሉዓላዊነት መጣስ ተደርገው እንዲቆጠሩ የማስፈራራትና የሐሰት ትረካና ዘመቻ ታካሂዳለች። ግብጽ የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት ላይ አንድ ወጥ አቋም እንዳይዙ ለማድረግ ድርጅቶቹን የፖለቲካ ፍልሚያ መድረክ በማድረግ የቀጣናውን ተቋማዊ ትብብር የማደናቀፍ ተግባር እያከናወነች ይገኛል። የግብጽ ሚዲያዎች የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ የ130 ሚሊዮን ሕዝብ የረጅም ጊዜ ሕልውና እና የትውልድ ጥያቄ መሆኑ እየታወቀ ጠባብ የፖለቲካ አጀንዳ በማስመሰል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲይዝ የማድረግ ስራ ላይ ተጠምደዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና (AfCFTA) ውስጥ የምታደርገውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ፣ የወደብ ትራንዚት ወጪዋ ከፍተኛ ሆኖ እንዲቀጥል በማድረግ ምርቶቿ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ጫና ለመፍጠር ትሰራለች። የግብጽ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን ለዘለቄታው የመልክዐ-ምድር እስረኛ አድርጎ በማስቀረት፣ በምሥራቅ አፍሪካ የሚኖራትን ጂኦ-ፖለቲካዊና የኢኮኖሚ የበላይነት መግታት ነው። ሆኖም የግብጽ ሴራ የኢትዮጵያን የልማት መንገድ ሊያስቆመው አይችልም። ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በሕዝቦቿ የማይበገር ጽናትና ቁርጠኝነት እውን እንደሆነ ሁሉ፤ በቀይ ባህር ላይ ህጋዊና ፍትሃዊ መብትን የማረጋገጥ ጉዞም የቀጣናውን የታሪክ ሂደት የሚቀይር የማይቀለበስ ብሔራዊ የህልውና ጉዳይ ነው።
ህገ-ወጡ የህውሓት ቡድን በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈፅመው ግፍና በደል ሊያበቃ ይገባል
Aug 19, 2026 133
ደብረ ብርሃን ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ ህገ-ወጡ የህውሓት ቡድን በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈፅመው ግፍና በደል ሊያበቃ ይገባል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የትግራይ ተወላጅ እናቶች ገለጹ። ህገ ወጡ የህወሃት ቡድን ከባንዳ እና ባዳዎች ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል ህዝቡን በማፈን በደሎችን እየፈጸመ ይገኛል። በተለይም እናቶች እያለቀሱ ታዳጊዎች እና ህፃናትን በግዳጅ ወደ ውትድርና ከማሰማራት ባለፈ ለሱዳን አሳልፎ በመሸጥ ጥቅሙን እያግበሰበሰ ያለ የወንጀለኞች ስብስብ ሆኗል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ካነጋገራቸው የትግራይ ተወላጅ እናቶች መካከል ወይዘሮ ትርሐስ መዝገቡ እና ወይዘሮ ፀጋ ኪዳኑ፤ የህገ-ወጡ ህውሃት ቡድን ግፍና በደል እየበረታ ህዝቡ ለስቃይና እንግልት እየተዳረገ ይገኛል ብለዋል። የህወሃት ቡድን የጥፋት ስብስብ ከህፃን እስከ አዋቂ በማፈንና በአስገዳጅነት ወደ ውትድርና በመውሰድ እናቶችን እያስለቀሰ መሆኑንም ተናግረዋል። በአረጀና በቆየ አስተሳሰብ እየተመራ ያለው ይህ ህገ-ወጥ ቡድን ለማንም የማይጠቅም የጥፋት ስብስብ መሆኑን ገልጸው የትግራይ ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሰላምና ልማትን ይሻል ብለዋል። በትግራይ አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር በመጣር ረገድ መንግስት ያደረገውን ተደጋጋሚ ጥረት ያደነቁት ወይዘሮ ትርሐስ፤ በክልሉ የነበረውን ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ ጭምር ህገ-ወጡ ህወሃት ምንም አይነት የሰላም ፍላጎት የሌለው መሆኑን በተግባር አሳይቷል ብለዋል። በመሆኑም የጥፋት ቡድኑ በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈፀመው ግፍና በደል እንዲያበቃ በጋራ መታገል ይገባናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ፀጋ ኪዳኑ፤ ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት አካታችና ሁሉን አቀፍ ምክክር እየተካሄደ ባለበት በዚህ ወቅት ህገ-ወጡ ህወሃት “ጽምዶ” እያለ ለጦርነት የሚያደርገው ዝግጅት እና የሀገር ክህደት ቡድኑ መቼም ቢሆን ሰላም ፈላጊ አለመሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። በጦርነት አዙሪት እድሜውን በማራዘም ከክልሉም ባለፈ የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም አሳልፎ ለመስጠት እየሰራ መሆኑን በግልጽ ማሳወቁን ያነሱት አስተያየት ሰጪዎቹ በተለይም የትግራይ ክልል ህዝብ ሊታገለውና በህግም ተጠያቂ ልናደርገው ይገባል ነው ያሉት።
ፌዴራል ፖሊስ የፀጥታ ስጋቶችን በላቀ ብቃት ለመመከት ዝግጁ ነው - ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል
Aug 19, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የፀጥታ ስጋቶችን በላቀ ብቃት በማክሸፍ የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገለጹ፡፡ የፌደራል ፖሊስ ስትራቴጂክ አመራሮችና ከፍተኛ የፖሊስ መኮንኖች በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፀጥታ እቅድ ዙሪያ መክረዋል፡፡   ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በዚህ ወቅት ተቋማቸው የሠራዊቱን ሥነ ልቦና በመገንባት፣ የወትሮ ዝግጁነት በማጠናከርና የማድረግ አቅሙን ይበልጥ በማሳደግ ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን የመጠበቅ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ እድገት እያሳየች ባለችበት ወቅት ሰላሟንና እድገቷን የማይፈልጉ አካላት የደቀኑትን የፀጥታ ስጋት ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍለን ለማክሸፍ ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡   በመድረኩ በሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ እና በወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ የመወያያ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት መሆኑንም የፌደራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡
መደመር የደረመሠው የጠላት ካምፕና የባንዳዎች እሪታ
Aug 19, 2026 304
በምስራቅ አፍሪካና በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የካይሮ እጅ ሁልጊዜም ኢትዮጵያን ማዕከል ያደረጉ እኩይ ስትራቴጂዎችን በመተለም ይታወቃል። የዓባይ ወንዝ ዋነኛ ምንጭና የተፈጥሮ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያን ማዳከም፣ የውስጥ ግጭቶችን ማበረታት እና በቀይ ባሕር እንዲሁም በኤደን ባሕረ-ሰላጤ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍላጎት ማደናቀፍ የግብፅ የረጅም ጊዜ የውጭ ፖሊሲ መሠረት ሆኖ ቆይቷል። ግብፅ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በወታደራዊ ኃይል ኢትዮጵያን በግልጽ ወርራ ለመቆጣጠር ባደረገችው ሙከራ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1875 በጉንደት እንዲሁም 1876 በጉራዕ ጦርነቶች በኢትዮጵያ አሳፋሪ ሽንፈት አስተናግዳለች ። ከዚህ የቀጥታ ወታደራዊ ሽንፈት በኋላ ካይሮ ኢትዮጵያን በግልጽ ጦርነት ማንበርከክ እንደማትችል ተረድታ ወደ ተዘዋዋሪ የውስጥ ሴራና የእጅ-አዙር ጦርነት ተሸጋግራለች። ካይሮ ኢትዮጵያ ጠንካራና የበለፀገች ሀገር ሆና ከተነሳች በዓባይ ውሃ ላይ ያላትን አጠቃላይ የበላይነት እንደምታጣ ስለሚሰማት፣ የሀገሪቱን እድገት የማደናቀፍና በጂኦፖለቲካው መስክ ወደብ አልባ አድርጎ የመዝጋት ስትራቴጂን ለዘመናት ስትከተል ኖራለች። ይህም የታሪክ እውነታ ከትላንት እስከ ዛሬ በስውርና በግልጽ የሴራ መረቦች ተሸርቦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሲፈታተን የኖረ መራራ እውነት ነው። የቡትሮስ ብትሮስ ጋሊ የዲፕሎማሲ ሽፋን እና ኢትዮጵያን ወደብ የማሳጣት ሴራ በታሪክ አጋጣሚዎች እንደምናየው፣ በግብፅ የፖለቲካ ልሂቃን የታቀዱ ሴራዎች በዓለም አቀፍ መድረኮች እንዴት ተግባራዊ እንደሆኑ አንደኛው ማሳያ የቀድሞው ግብፃዊ ዲፕሎማት ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ አካሄድ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በ1970ዎቹ መጨረሻ በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራር በነበሩበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ በውስጥ ግጭት እንድትታመስና የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ ስጋት እንዳትሆን ከበስተጀርባ የዓመፅ ኃይሎችን የማጠናከር ስራ ሲሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ሃቅ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በውሃ ፖለቲካ ረገድ በሰጡት የታወቀ ንግግራቸው “ቀጣዩ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና የሚካሄደው ጦርነት በፖለቲካ ምክንያት ሳይሆን በውሃ ምክንያት የሚደረግ ይሆናል” በማለት ለቀጣናው ያሰቡ መስለው የካይሮን የውሃ የበላይነት ስጋትና ፍላጎት በግልጽ አንጸባርቀው ነበር። ይህ ንግግራቸው ግብፅ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት የመቆጣጠር ፍላጎቷንና ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ የልማት ፕሮጀክቶችን እንዳታካሂድ ለማድረግ የምታደርገው ሴራ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲያገኝ ዓላማ ያደረገ አደገኛ ንግግር ነው። በኋላም እ.ኤ.አ በ1993 ኤርትራን ከኢትዮጵያ በመገንጠል ሂደት ውስጥ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የስድስተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ ነበሩ። በወቅቱ 99 ነጥብ 8% የሚሆኑት ኤርትራዊያን በሕዝበ ውሳኔ ነጻ ሀገርንትን መርጠዋል በሚል ሕወሃትና ሻዕቢያ የሰሩት ድራማ ተቀባይነት አንዲያገኝ የተመድ ዋና ጸሐፊው ከፍተኛ ሴራ ሰርተዋል። ይህ የኤርትራ ህዝብን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በሻዕቢያ ባርነትና ግዞት እንዲማቅቅ ያደረገው የሕዝበ ውሳኔ ድራማ ላይ ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊ የመሪ ተዋናይነትን ሚና ተጫውተዋል። በሂደቱም ዋነኛ ዓላማቸው የሆነውን ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በሯን እንድታጣ አድርገዋል። ይህም የካይሮ የረጅም ጊዜ “ኢትዮጵያን የመዝጋት” ስትራቴጂ አካል እንደነበር ግልጽ ነው። የካይሮ መጥረቢያ እና አሁናዊው የጥፋት መንገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት የመጥረቢያ ተምሳሌታዊ ማብራሪያ፣ ሕገ ወጡ ሕወሃትን እንደ መጥረቢያ ብረት፤ ሻዕቢያን ደግሞ እንደ መጥረቢያ ዛቢያ ያስቀመጡ ሲሆን፤ መጥረቢያውን የሚያዘውና የሚወረውረው ሌላ ሶስተኛ አካል መኖሩንም ተናግረዋል። እንደሚታወቀው መጥረቢያ አንድን ነገር የመቁረጥና የማፍረስ ስራ ለማከናወን የሶስት አካላት ቅንጅት ያስፈልገዋል፦ ወርዋሪው (እጁ)፣ ዛቢያው (መያዣው) እና ብረቱ (ቁራጩ)። በዚህ ተምሳሌት ውስጥ ወርዋሪው ወይም መጥረቢያውን ጨብጦ ስራ ላይ የሚያውለው አካል ግብፅ ናት። ወርዋሪው ሁልጊዜም ከበስተጀርባ ሆኖ ስትራቴጂ ይነድፋል፣ ፋይናንስና ወታደራዊ ድጋፍ ያቀርባል፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሽፋን ይሰጣል። በሌላ በኩል የመጥረቢያ ብረት ያለ ዛቢያው (መያዣው) ኃይል አግኝቶ ማረፍ አይችልም፤ ዛቢያውም ያለ ወርዋሪው እጅ መንቀሳቀስ አይችልም። በዚህ ሂደት ሻዕቢያ (እንደ ዛቢያ) በቀጣናው ውስጥ የካይሮን ፍላጎት ለማስፈጸም የመያዣነት ሚና ይጫወታል። ቀጣናውን ለማተራመስ በሞመከር የካይሮን ስትራቴጂካዊ ፍላጎት ለማሳካት መንገድ ይከፍታል። ህገ-ወጡ ህወሓት ደግሞ እንደ መጥረቢያ ብረት በሀገር ውስጥ ሆኖ የሀገሪቱን መዋቅር፣ የህዝቦችን አንድነት እና ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ጥቅም ለመሸርሸር የሚሰራ ተላላኪ መሳሪያ ነው። በዚህ የሴራ ትስስር አሁን ላይ ኢትዮጵያ በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት ማደናቀፍ ዋነኛ ዓላማው አድርጎም እየሰራ ይገኛል። ግብፅ “የቀይ ባሕርና የኤደን ባሕረ-ሰላጤ የባሕር ወሰን ያላቸው ሀገራት ብቻ ናቸው በውሃው ላይ መወሰን ያለባቸው” የሚል መርህ በማንሳት፣ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትንና በቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኘውን ትልቁን ኢኮኖሚ (ኢትዮጵያን) ያገለለ ህገ-ወጥ ስብስብ ለመፍጠር እየሰራች ነው። በተጨማሪም በቅርቡ ከሶማሊያና ከሌሎች የአካባቢው ሀገራት ጋር የተደረጉ የውትድርናና የደህንነት ስምምነቶች፣ የሶማሊያን ሰላም ለማስጠበቅ ሳይሆን ቀጣናውን ለማተራመስና ወታደራዊ ስጋት ለመፍጠር የተቃኙ ናቸው። ይህ ሁሉ አካሄድ ዋነኛ ዓላማው ቀጣናውን የውክልና ጦርነት ማዕከል በማድረግና ኢትዮጵያ ወደ ባሕር እንዳትቀርብ ሆነ ተብሎ የተሰላ ሴራ ነው። ከቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ እስከ ዛሬው የቀይ ባሕር ሴራዎች ድረስ የተዘረጉት መረቦችም ይህንኑ እውነት ያሳያሉ። የካይሮ መጥረቢያዎችን ያዶለዶመው የመደመር መንግሥት ጥንካሬ ግብጽ እያከናወነችው ባለው አሁናዊ ሴራ ውስጥ የካይሮ ስትራቴጂስቶች የሳቱት ትልቅ እውነታ አለ። የግብጽ የሴራ መጥረቢያዎች ለመቁረጥ የሚሞክሩት በፈተናዎች የማትበገረውን እና እንደ ወርቅ በእሳት ውስጥ ተፈትና ያለፈችውን ኢትዮጵያን መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በታሪኳ የውጭ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎችን አሸንፎ መውጣት እንግዳ የሆነባት ሀገር አይደለችም። ባለፉት ክፍለ ዘመናት በወረራ፣ በውስጥ አለመረጋጋትና በጂኦፖለቲካዊ ከበባዎች ውስጥ አልፋ የጸናች ሀገር ናት። ወርቅ በእሳት ውስጥ ሲያልፍ ቆሻሻው ተወግዶ ይበልጥ እንደሚበራ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በተጋረጡባት የህልውና ፈተናዎች ሁሉ አልፋ ይበልጥ እየጠነከረችና እየተደራጀች መምጣቷ የታሪክ እውነታ ነው። አሁን ባለንበት ዘመን ደግሞ ይህ ጥንካሬዋ ይበልጥ ጎልብቷል። የመደመር መንግሥት ቁልፍ ፍልስፍና እና እየተገበራቸው ያሉ እርምጃዎች የካይሮን የረጅም ጊዜ የእጅ አዙር ጦርነትና ሴራዎችን ከንቱ ያደረገ ነው። የመደመር መንግሥት የውጭ ጫናዎችንና ሴራዎችን ለመመከት የመጀመሪያው ምሽግ የውስጥ አቅምን ማጠናከር መሆኑን በመገንዘብ፣ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለፍፃሜ ማብቃትና ግዙፍ የግብርና፣ የአረንጓዴ አሻራ እና የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን እውን አድርጓል። ይህም ግብፅ ኢትዮጵያን በልማት እንዳትበለፅግ ለማድረግ ያቀደችውን ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ አክሽፎታል። ካይሮ ኢትዮጵያን በጂኦፖለቲካዊ ከበባ ለማዳከምና በውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የነደፈችው የረጅም ጊዜ የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት ባስመዘገባቸው የልማትና የዲፕሎማሲ ድሎች ምክንያት ሙሉ በሙሉ ተደርምሷል። ይህ የጠላት ካምፕ መደርመስና የኪሳራ ስሌት ደግሞ በካይሮ ስትራቴጂስቶችና በውስጥ ተላላኪዎቻቸው (ባንዳዎች) ዘንድ ታላቅ ድንጋጤንና ተስፋ የመቁረጥ እሪታን ፈጥሯል። በመሆኑም የተበተነው የጠላት ካምፕና የተበሳጩት ባንዳዎች ብቸኛ አማራጭ አድርገው የያዙት በሳይበርና በሚዲያ ምህዳር የሃሰት መረጃዎችን ማንደድና የፕሮፓጋንዳ ማዕበል መፍጠር ቢሆንም፣ ይህም የተስፋ መቁረጥ ድምፅ ብክለት እንጂ የኢትዮጵያን የጽናት ጉዞ የሚያስተጓጉል አይሆንም። በሌላ በኩል ግብፅ “የቀይ ባሕር ሀገራት ጥምረት” በሚል ስም ቀጣናውን ለማተራመስና እርስ በርስ ጥርጣሬ ለመፍጠር የምታደርገውን የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት የጋራ እድገትና የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በማስቀደም በዲፕሎማሲው መስክ እየመከተው ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ምክክር የጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ በጋራ እንዲወስኑ በማድርግም የካይሮ ስትራቴጂስቶች በኢትዮጵያ የውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የጠነሰሱትን ሴራ ከንቱ አድርጎታል። በአጠቃላይ ታሪክ እንደሚነግረንና የወቅቱ እውነታ እንደሚመሰክረው፣ የግብፅ የሴራ መጥረቢያዎች በፈተናዎች እሳት ተፈትና ባላለፈች ደካማ ሀገር ላይ ያረፉ አይደሉም። ለመቁረጥ የሞከሩት በጽናት፣ በህዝቦቿ መስዋዕትነትና በፅኑ ታሪካዊ መሰረት ላይ የቆመችውን ኢትዮጵያን ነው። አሁን ላይ በመደመር መንግሥት መሪነት እየተገነባ ያለው የውስጥ አቅም፣ የልማት ስኬትና በራስ መተማመን የካይሮን የረጅም ጊዜ የከበባ ሴራ ሙሉ በሙሉ ወድቅ ማድረጉን ቀጥሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ሁሉ አሸንፎ ማለፍ የሰርክ ተግባሯ እንደመሆኑ መጠን፣ የዛሬውንም የጂኦፖለቲካ ውጥረትና የሴራ መረብ በጽናት አልፋ የቀጣናው የልማትና የሰላም ማዕከል ሆና መቀጠሏ የማይቀየር እውነት ነው።
ምክክሩ ኢትዮጵያን ማጽናት የሚያስችል ትልቅ መሰረት እየጣለ ይገኛል-ተመካካሪዎች
Aug 19, 2026 152
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ) ፦ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያን በጠንካራ የተግባቦት ዓለት ላይ ለማጽናት ትልቅ መሰረት እየጣለ እንደሚገኝ ተመካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ለዘመናት በኢትዮጵያ የዘለቁ አለመግባባቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት፣ኢትዮጵያዊያን ካለፈው ኋላቀር እሳቤ በመላቀቅ ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እያደረጉ ይገኛል። ይህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 4 ሺህ ኢትዮጵያውያን እየተመካከሩበት በሚገኘው በዚህ ጉባኤ፣የተመካካሪዎች ሀሳብ በነጻነት የሚንሸራሸርበት ነጻ እና ዴሞክራሲያዊ አውድ ተፈጥሯል። በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሄደ ያለው ይህ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያን በጠንካራ የተግባቦት ዓለት ላይ ለማጽናት ትልቅ መሰረት የሚጥል መሆኑን ከፖለቲካ ፓርቲዎች የተወከሉ ተመካካሪዎች ለኢዜአ ገልጸዋል። ከተመካካሪዎች መካከል የአፋር ነጻ አውጪ ግንባርን ወክለው የመጡት ሀጂ እስማኤል መሀመድ እንዳሉት፣የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በማካተት በሰለጠነ አግባብ እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ ተመካካሪዎች ሃሳባቸውን በነጻነት የሚያንሸራሽሩበት በመሆኑ ዘላቂ ሰላም እና ሀገራዊ መግባባትን ለማስፈን ትልቅ ዕድል እየፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተወክለው የሚወያዩበት ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ የሀገሪቱን የልማት እና የዴሞክራሲ ጉዞ ለማቀላጠፍም ወሳኝ ምዕራፍ እንደሚከፍት ተናግረዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ የሲዳማ አርነት ንቅናቄን ወክለው በመሳተፍ ላይ ያሉት ደምሴ ስኳሬ ፣ የምክክር ሂደቱ ከመነሻው ጀምሮ ግልጽነትና አሳታፊነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሂደቱ ከታች ጀምሮ የተለያዩ ሀሳቦችን በማብሰልና በማዋሃድ ወደ ላቀ የጋራ ሀገራዊ መግባባት የሚያደርስ እና ይህም የሂደቱን የሰለጠነ አካሄድ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ምክክሩ ለሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የመላው ተመካካሪዎች ድምፅ በነጻነት የተደመጠበት ሁሉን አቀፍ ጉባኤ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን በመወከል በመሳተፍ ላይ ያሉት ተመካካሪ ነጻነት ጣሰው ናቸው።   ተመካካሪዎች እርስ በርሳቸው እንዲተዋወቁና ጠንካራ አዎንታዊ ግንኙነት እንዲፈጥሩ ሰፊ ዕድል በመፍጠር ሂደት ውስጥ ልዩ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግረዋል። መድረኩ ኢትዮጵያን የሚያሻግሩ ገንቢ ሀሳቦች እየተነሱበት በመሆኑ የመደማመጥ እና የጋራ መግባባት ባህልን ለማጠናከር ትልቅ አጋጣሚ መፈጠሩንም አንስተዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች መካተታቸው የተሻለች ሀገር በጋራ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል።
ከምክክር ጉባዔው ለፖለቲካዊ አለመግባባቶች መፍትሔ የሚሆኑ ምክረ ሃሳቦችን እንጠብቃለን - የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች
Aug 19, 2026 156
አዳማ፤ ነሐሴ 13/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ለፖለቲካዊ አለመግባባቶች መፍትሔ የሚሆኑ ምክረ ሃሳቦችን ይሰጣል የሚል ትልቅ እምነት እንዳላቸው የአዳማ ከተማ አባ ገዳ እና የሃይማኖት አባት ተናገሩ። ከሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡት የአዳማ ከተማ አባ ገዳ እና የሃይማኖት አባት፣ አካታችነቱና አሳታፊነቱ ጎልቶ የታየው የሀገራዊ ምክክር ጉባዔው በፖለቲካዊ አለመግባባቶች ላይ ዘላቂ መፍትሔና ምክረ ሃሳቦችን ያመጣል የሚል ትልቅ እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። በአዳማ ከተማ የቦኩ ክፍለ ከተማ አባገዳ ተሾመ ስማ እንደገለፁት ሀገራዊ ምክክሩ በዘመናት ውስጥ ሀገራችን ያገኘችው ታሪካዊ ድል ነው ብለዋል። ተመካካሪዎች ህዝቡን ወክለው ለኢትዮጵያ የተሻለ መፍትሔ ለማስቀመጥ እየመከሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ በሀገሪቱ በህዝቦች መካከል የቆዩ ቅሬታዎችንና ቁርሾዎችን በመሻር ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ትልቅ መሰረት እንደሚጥል ተስፋ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። መንግሥትም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር ጉባዔውን ምክረ ሀሳቦች በማክበርና ወደ ተግባር በመለወጥ ረገድ መተባበር እንዳለባቸው ገልጸዋል። ሀገራችንና ህዝባችን ይህንን እድል በማግኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን የገለጹት አባገዳው፤ ከምክክር ጉባዔው ትልቅ ውጤት እንደሚጠብቁም አክለው ተናግረዋል። የአዳማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አባል ሼህ አብዱልቃድር አህመድ እንደገለፁት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የነበሩ ቁርሾዎችን በሁለንተናዊ መልኩ እንደሚፈታ ተስፋ አድርገዋል። በተለይም በሀገሪቱ የነበሩትን የፖለቲካ አለመግባባቶች ለመቅረፍ ብቸኛው መፍትሔ ምክክር መሆኑን ገልጸዋል። በምክክሩ ጥሩ መፍትሔ ይመጣል የሚል ተስፋ እንዳላቸው የገለጹት ሼህ አብዱልቃድር፤ ለተፈጻሚነቱ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንደሚወጡም ተናግረዋል። ምሁራን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የቀድሞ ታጣቂዎች፣ የሃይማኖት ተወካዮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የፀጥታ አካላት እንዲሁም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት የምክክር ጉባዔ በመሆኑን ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ አጀንዳ ከማሰባሰብ ጀምሮ ሁሉንም ያማከለ፣ አሳታፊና አካታች እንደነበር የገለጹት ሼህ አብዱልቃድር፤ ሂደቱ ለሀገራችን ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያመጣ ሙሉ እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
በምክክር ጉባኤው ምክረ ሀሳቦች የተጠናቀረው የመጨረሻ ሰነድ ነገ ለአራት ሺህ ተመካካሪዎች በጋራ ይቀርባል-ኮሚሽኑ
Aug 19, 2026 205
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በቀረቡ ምክረ ሀሳቦች ላይ የተጠናቀረው የመጨረሻ ሰነድ ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ለአራት ሺህ ተመካካሪዎች በጋራ እንደሚቀርብ አስታወቀ። የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገብረሥላሴ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን አሁናዊ ሁኔታ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ ከስምንቱም ቡድኖች የቀረበውን ምክረ ሀሳብ ለማጣጣም የተቋቋመው 120 አባላት ያሉት አጠናቃሪ ቡድን በጥንቃቄ ሲሰራ ቆይቶ እስከ ትናንት ምሽት ድረስ አንድ ወጥ የሆነ ሰነድ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል። እንደ ኮሚሽነሯ ገለጻ፣ የተዘጋጀው ሰነድ ዛሬ ጠዋት ለየስምንቱ ቡድኖች የቀረበ ሲሆን፣ ቡድኖቹ ሰነዱን አዳምጠው የመጨረሻ ግብዓትና አስተያየት እየሰጡ እንደሚገኝ አመልክተዋል። አጠናቃሪ ቡድኑ ዛሬ ማምሻውን እነዚህን የተሰበሰቡ አስተያየቶች በማካተት የመጨረሻውን ሰነድ አጠናቆ እንደሚያዘጋጅ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የተጠናቀረው የመጨረሻ ሰነድ ለአራት ሺህ የጉባኤው ተሳታፊዎች በጋራ የሚቀርብ ሲሆን፣ይህም ሂደቱ ትልቅ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የሚያመላክት ነው ብለዋል። ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ህዝቡ አንዳንዶች የሚያሰራጩትን የተዛባ መረጃ በመስማት እንዳይወዛገብ እና ለትክክለኛ መረጃዎች የኮሚሽኑን መግለጫዎች ብቻ እንዲከታተል አሳስበዋል።
ምክክሩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የሀገሪቱ መፃኢ እድል ብሩህ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን-ነዋሪዎች
Aug 19, 2026 169
ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የሀገሪቱ መፃኢ እድል ብሩህ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የቦንጋና ታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ለዘመናት ለቆዩ አለመግባባቶች መንስኤ የሆኑ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ በጋራ መክሮ ለመፍታት እንደሚያስችል የታመነበት የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል። አካታችና አሳታፊነቱ ጎልቶ የታየበት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በታሪክ የታየውን ልዩነት በሰለጠነ መንገድ በመወያየት የሚሰጣቸው የመፍትሔ ሀሳቦች ሀገራዊ መግባባትን እንደሚፈጥሩ በህዝቦች ዘንድ ተስፋ ተጥሎበታል። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋና የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ሀገራዊ ምክክሩ የነበሩ አለመግባባቶችን በውይይትና በምክክር በመፍታት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። ነዋሪዎቹ አክለውም፤ ምክክሩ ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የሀገሪቱ መፃኢ እድል ብሩህ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል። የቦንጋ ከተማ ነዋሪው አቶ ታሪኩ ታዬ፤ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር ታሪካዊና ለረጅም ዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የሀገራችንን መፃኢ እድል የሚወስን መሆኑን ተናግረዋል። ከአራቱም የሀገሪቱ አቅጣጫዎች የተወከሉ ኢትዮጵያውያን በጋራ ቁጭ ብለው በጠረጴዛ ዙሪያ መምከራቸው በሀገራቸው ጉዳይ ያገባኛል የሚል እምነት እንዲኖራቸውና የመፍትሔው አካል መሆን የሚያስችላቸው ትልቅ እድል እንደሆነም ገልጸዋል። እንደ አቶ ታሪኩ ገለጻ፤ ምክክሩ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለአፍሪካ ሰላምና አንድነት ፋና ወጊ ሀገር ሆና ሳለች የውስጥ ችግሮቿን በውይይትና በምክክር መፍታት ተስኗት የቆየችበትን ታሪክ በማደስ ወደ አዲስ ምዕራፍ የምትሸጋገርበት ትልቅ ዕድል ነው። የምክክር መድረኩ ለዘመናት ሳይፈቱ የቆዩ ውስብስብ ችግሮችን ተወያይቶ ለመፍታትና ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር የሀገርን ሰላምና እድገት እንደሚያጠናክር ተስፋቸውን የገለጹት ሌላኛው የቦንጋ ከተማ ነዋሪ አቶ ደመረ ጌታሁን ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያውያን በተወካያቸው አማካይነት የተሳተፉበት መሆኑ ለሀገር ሰላምና ብልፅግና በአንድነት መቆም የሚያስችል ውጤት እንደሚያመጣ እምነታቸው መሆኑን ነው የገለጹት። በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ነዋሪው አቶ አብርሃም አሳሮ በበኩላቸው፤ ምክክሩ እየተካሄደባቸው ባሉት አጀንዳዎች የሚደረሱ ውጤቶች በኢትዮጵያ የነበሩ በርካታ አለመግባባቶች፣ መቃቃሮችና አለመደማመጦችን በዘላቂነት የሚፈቱ እንደሚሆኑ እምነታቸው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ እየተካሄደ መሆኑ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄዎችና ሐሳቦች በተወካዮቻቸው በኩል እንዲነሱ ያስቻለ በመሆኑ አንድነትንና አብሮነትን በማጠናከር ሀገራዊ መግባባትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ምክክሩ እኔ የሚለውን ነጠላ ትርክት እኛ በሚለው የወል ትርክት በመተካት ሀገራዊ እይታን ያጎላል ያሉት አቶ አብርሃም፤ ይህም ኢትዮጵያውያን ለሀገር ሰላምና ልማት በጋራ መቆም የሚያስችላቸው ወርቃማ እድል መሆኑን ጠቁመዋል። ሀገራዊ ምክክሩ አለመግባባቶችንና ችግሮችን ከምንጫቸው በሰለጠነ መንገድ በውይይት በመፍታት በአብሮነትና በአንድነት ወደፊት ለመራመድ ያስችለናል ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ዘሪሁን ለማ ናቸው። ኢትዮጵያ የረጅም ዘመናት ታሪክና ችግሮቿን በውስጥ አቅም መፍታት የሚያስችሏት የበርካታ ሀገር በቀል እውቀቶች ባለቤት መሆኗን የገለጹት አቶ ዘሪሁን፤ ምክክሩ በዚህ ላይ የተመሰረተና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ትልቅ ተስፋን የያዘ አዲስ ምዕራፍ ነው ብለዋል።
ፖለቲካ
የግብጽ እኩይ ሴራ የማይገታው የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት መብት
Aug 19, 2026 175
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች የምትገኘው እና የቀጣናው የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋት ዋና መሠረት ነች። የኢትዮጵያ፣ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የፖለቲካ ፍላጎት ሳይሆን ሀገራዊ ሕልውናንና ደህንነትን የማረጋገጥ፣ የልማትና ብልጽግናን ዕውን የማድረግ የትውልድ ጥያቄ ነው። ትልቅ አቅም ያላት ኢትዮጵያ በመልክዐ-ምድራዊ እስር ውስጥ እንድትቀር የሚደረገው ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍትሕን የሚቃረን አካሄድን ለማረም ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት የነበራት የባህር በር ባለቤትነት እና የማሪታይም መብት በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እየሰራች ነው። ይህ የኢትዮጵያ ፍትሐዊና የማይቀረው የሕልውና ጥያቄ በዓለም አቀፉ የባሕር ሕግ ኮንቬንሽን (UNCLOS) የተረጋገጠ እና በጋራ ተጠቃሚነት (Win-Win) መርሕ ላይ የተመሠረተ ቢሆንም፣ የግብጽ ፖሊሲ አውጪዎች ግን ይህንን የሕልውና ጥያቄ ለማክሸፍ የሴራ እና የከበባ ስትራቴጂያቸውን ለማስፈጸም እየሰሩ ይገኛሉ። የግብጽ ሴራ በዋናነት ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ለወደብ ኪራይ እንድታወጣ በማስገደድ፣ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት የሚወጣው ካፒታል እንዲሟጠጥ በማድረግ የሀገሪቱን የኢንዱስትሪያላይዜሽንና የልማት ዕድገት ለማቀጨጭ ያለመ የኢኮኖሚ ዘመቻ ነው። በተጨማሪም ግብጽ የቀይ ባሕርን ማሪታይም ቀጣና “የባሕር ዳርቻ ሀገራት ብቻ (Littoral States) ይዞታ" አድርጋ በመሳል፣ የኢትዮጵያን ታሪካዊና ሕጋዊ የመጠቀም መብት በመካድ ከማንኛውም የቀይ ባሕር የደህንነትና የኢኮኖሚ ስብስብ እንድትገለል እየሰራች ትገኛለች። ግብጽ ከኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርጋቸው ወታደራዊ ስምምነቶች በሰሜንና በምሥራቅ ድንበሮች አካባቢ አዲስ የደህንነት ስጋት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ ሀብቷንና ትኩረቷን ወደ የብስ ጥበቃ እንድታዞርና ለባህር ኃይል ግንባታ የምታውለውን አቅም እንድታበታትን የታለመ የከበባ ስልትም ነው። በዓለም አቀፍ የፋይናንስና የኢንቨስትመንት ተቋማት ዘንድ የምታደርገው የዲፕሎማሲ ጫና፣ ኢትዮጵያ ለወደብ እና ለትራንስፖርት ኮሪደሮች ልማት የሚሆን የውጭ ኢንቨስትመንት እንዳታገኝ እና የቀይ ባሕር አካባቢ የስጋት ቀጠና ተደርጎ እንዲቆጠር በማድረግ ኢንቨስተሮች እንዲሸሹ በማድረግ ላይ ናት። በጎረቤት ሀገራት ዘንድ የጥርጣሬ እና የስጋት ግንብ በመገንባት፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር የምታደርጋቸው ፍትሐዊና የጋራ ዕድገትን ያለሙ የወደብ ስምምነቶች የሉዓላዊነት መጣስ ተደርገው እንዲቆጠሩ የማስፈራራትና የሐሰት ትረካና ዘመቻ ታካሂዳለች። ግብጽ የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት ላይ አንድ ወጥ አቋም እንዳይዙ ለማድረግ ድርጅቶቹን የፖለቲካ ፍልሚያ መድረክ በማድረግ የቀጣናውን ተቋማዊ ትብብር የማደናቀፍ ተግባር እያከናወነች ይገኛል። የግብጽ ሚዲያዎች የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ የ130 ሚሊዮን ሕዝብ የረጅም ጊዜ ሕልውና እና የትውልድ ጥያቄ መሆኑ እየታወቀ ጠባብ የፖለቲካ አጀንዳ በማስመሰል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲይዝ የማድረግ ስራ ላይ ተጠምደዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና (AfCFTA) ውስጥ የምታደርገውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ፣ የወደብ ትራንዚት ወጪዋ ከፍተኛ ሆኖ እንዲቀጥል በማድረግ ምርቶቿ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ጫና ለመፍጠር ትሰራለች። የግብጽ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን ለዘለቄታው የመልክዐ-ምድር እስረኛ አድርጎ በማስቀረት፣ በምሥራቅ አፍሪካ የሚኖራትን ጂኦ-ፖለቲካዊና የኢኮኖሚ የበላይነት መግታት ነው። ሆኖም የግብጽ ሴራ የኢትዮጵያን የልማት መንገድ ሊያስቆመው አይችልም። ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በሕዝቦቿ የማይበገር ጽናትና ቁርጠኝነት እውን እንደሆነ ሁሉ፤ በቀይ ባህር ላይ ህጋዊና ፍትሃዊ መብትን የማረጋገጥ ጉዞም የቀጣናውን የታሪክ ሂደት የሚቀይር የማይቀለበስ ብሔራዊ የህልውና ጉዳይ ነው።
ህገ-ወጡ የህውሓት ቡድን በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈፅመው ግፍና በደል ሊያበቃ ይገባል
Aug 19, 2026 133
ደብረ ብርሃን ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ ህገ-ወጡ የህውሓት ቡድን በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈፅመው ግፍና በደል ሊያበቃ ይገባል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የትግራይ ተወላጅ እናቶች ገለጹ። ህገ ወጡ የህወሃት ቡድን ከባንዳ እና ባዳዎች ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል ህዝቡን በማፈን በደሎችን እየፈጸመ ይገኛል። በተለይም እናቶች እያለቀሱ ታዳጊዎች እና ህፃናትን በግዳጅ ወደ ውትድርና ከማሰማራት ባለፈ ለሱዳን አሳልፎ በመሸጥ ጥቅሙን እያግበሰበሰ ያለ የወንጀለኞች ስብስብ ሆኗል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ካነጋገራቸው የትግራይ ተወላጅ እናቶች መካከል ወይዘሮ ትርሐስ መዝገቡ እና ወይዘሮ ፀጋ ኪዳኑ፤ የህገ-ወጡ ህውሃት ቡድን ግፍና በደል እየበረታ ህዝቡ ለስቃይና እንግልት እየተዳረገ ይገኛል ብለዋል። የህወሃት ቡድን የጥፋት ስብስብ ከህፃን እስከ አዋቂ በማፈንና በአስገዳጅነት ወደ ውትድርና በመውሰድ እናቶችን እያስለቀሰ መሆኑንም ተናግረዋል። በአረጀና በቆየ አስተሳሰብ እየተመራ ያለው ይህ ህገ-ወጥ ቡድን ለማንም የማይጠቅም የጥፋት ስብስብ መሆኑን ገልጸው የትግራይ ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሰላምና ልማትን ይሻል ብለዋል። በትግራይ አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር በመጣር ረገድ መንግስት ያደረገውን ተደጋጋሚ ጥረት ያደነቁት ወይዘሮ ትርሐስ፤ በክልሉ የነበረውን ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ ጭምር ህገ-ወጡ ህወሃት ምንም አይነት የሰላም ፍላጎት የሌለው መሆኑን በተግባር አሳይቷል ብለዋል። በመሆኑም የጥፋት ቡድኑ በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈፀመው ግፍና በደል እንዲያበቃ በጋራ መታገል ይገባናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ፀጋ ኪዳኑ፤ ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት አካታችና ሁሉን አቀፍ ምክክር እየተካሄደ ባለበት በዚህ ወቅት ህገ-ወጡ ህወሃት “ጽምዶ” እያለ ለጦርነት የሚያደርገው ዝግጅት እና የሀገር ክህደት ቡድኑ መቼም ቢሆን ሰላም ፈላጊ አለመሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። በጦርነት አዙሪት እድሜውን በማራዘም ከክልሉም ባለፈ የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም አሳልፎ ለመስጠት እየሰራ መሆኑን በግልጽ ማሳወቁን ያነሱት አስተያየት ሰጪዎቹ በተለይም የትግራይ ክልል ህዝብ ሊታገለውና በህግም ተጠያቂ ልናደርገው ይገባል ነው ያሉት።
ፌዴራል ፖሊስ የፀጥታ ስጋቶችን በላቀ ብቃት ለመመከት ዝግጁ ነው - ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል
Aug 19, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የፀጥታ ስጋቶችን በላቀ ብቃት በማክሸፍ የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገለጹ፡፡ የፌደራል ፖሊስ ስትራቴጂክ አመራሮችና ከፍተኛ የፖሊስ መኮንኖች በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፀጥታ እቅድ ዙሪያ መክረዋል፡፡   ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በዚህ ወቅት ተቋማቸው የሠራዊቱን ሥነ ልቦና በመገንባት፣ የወትሮ ዝግጁነት በማጠናከርና የማድረግ አቅሙን ይበልጥ በማሳደግ ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን የመጠበቅ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ እድገት እያሳየች ባለችበት ወቅት ሰላሟንና እድገቷን የማይፈልጉ አካላት የደቀኑትን የፀጥታ ስጋት ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍለን ለማክሸፍ ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡   በመድረኩ በሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ እና በወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ የመወያያ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት መሆኑንም የፌደራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡
መደመር የደረመሠው የጠላት ካምፕና የባንዳዎች እሪታ
Aug 19, 2026 304
በምስራቅ አፍሪካና በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የካይሮ እጅ ሁልጊዜም ኢትዮጵያን ማዕከል ያደረጉ እኩይ ስትራቴጂዎችን በመተለም ይታወቃል። የዓባይ ወንዝ ዋነኛ ምንጭና የተፈጥሮ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያን ማዳከም፣ የውስጥ ግጭቶችን ማበረታት እና በቀይ ባሕር እንዲሁም በኤደን ባሕረ-ሰላጤ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍላጎት ማደናቀፍ የግብፅ የረጅም ጊዜ የውጭ ፖሊሲ መሠረት ሆኖ ቆይቷል። ግብፅ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በወታደራዊ ኃይል ኢትዮጵያን በግልጽ ወርራ ለመቆጣጠር ባደረገችው ሙከራ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1875 በጉንደት እንዲሁም 1876 በጉራዕ ጦርነቶች በኢትዮጵያ አሳፋሪ ሽንፈት አስተናግዳለች ። ከዚህ የቀጥታ ወታደራዊ ሽንፈት በኋላ ካይሮ ኢትዮጵያን በግልጽ ጦርነት ማንበርከክ እንደማትችል ተረድታ ወደ ተዘዋዋሪ የውስጥ ሴራና የእጅ-አዙር ጦርነት ተሸጋግራለች። ካይሮ ኢትዮጵያ ጠንካራና የበለፀገች ሀገር ሆና ከተነሳች በዓባይ ውሃ ላይ ያላትን አጠቃላይ የበላይነት እንደምታጣ ስለሚሰማት፣ የሀገሪቱን እድገት የማደናቀፍና በጂኦፖለቲካው መስክ ወደብ አልባ አድርጎ የመዝጋት ስትራቴጂን ለዘመናት ስትከተል ኖራለች። ይህም የታሪክ እውነታ ከትላንት እስከ ዛሬ በስውርና በግልጽ የሴራ መረቦች ተሸርቦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሲፈታተን የኖረ መራራ እውነት ነው። የቡትሮስ ብትሮስ ጋሊ የዲፕሎማሲ ሽፋን እና ኢትዮጵያን ወደብ የማሳጣት ሴራ በታሪክ አጋጣሚዎች እንደምናየው፣ በግብፅ የፖለቲካ ልሂቃን የታቀዱ ሴራዎች በዓለም አቀፍ መድረኮች እንዴት ተግባራዊ እንደሆኑ አንደኛው ማሳያ የቀድሞው ግብፃዊ ዲፕሎማት ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ አካሄድ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በ1970ዎቹ መጨረሻ በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራር በነበሩበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ በውስጥ ግጭት እንድትታመስና የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ ስጋት እንዳትሆን ከበስተጀርባ የዓመፅ ኃይሎችን የማጠናከር ስራ ሲሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ሃቅ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በውሃ ፖለቲካ ረገድ በሰጡት የታወቀ ንግግራቸው “ቀጣዩ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና የሚካሄደው ጦርነት በፖለቲካ ምክንያት ሳይሆን በውሃ ምክንያት የሚደረግ ይሆናል” በማለት ለቀጣናው ያሰቡ መስለው የካይሮን የውሃ የበላይነት ስጋትና ፍላጎት በግልጽ አንጸባርቀው ነበር። ይህ ንግግራቸው ግብፅ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት የመቆጣጠር ፍላጎቷንና ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ የልማት ፕሮጀክቶችን እንዳታካሂድ ለማድረግ የምታደርገው ሴራ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲያገኝ ዓላማ ያደረገ አደገኛ ንግግር ነው። በኋላም እ.ኤ.አ በ1993 ኤርትራን ከኢትዮጵያ በመገንጠል ሂደት ውስጥ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የስድስተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ ነበሩ። በወቅቱ 99 ነጥብ 8% የሚሆኑት ኤርትራዊያን በሕዝበ ውሳኔ ነጻ ሀገርንትን መርጠዋል በሚል ሕወሃትና ሻዕቢያ የሰሩት ድራማ ተቀባይነት አንዲያገኝ የተመድ ዋና ጸሐፊው ከፍተኛ ሴራ ሰርተዋል። ይህ የኤርትራ ህዝብን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በሻዕቢያ ባርነትና ግዞት እንዲማቅቅ ያደረገው የሕዝበ ውሳኔ ድራማ ላይ ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊ የመሪ ተዋናይነትን ሚና ተጫውተዋል። በሂደቱም ዋነኛ ዓላማቸው የሆነውን ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በሯን እንድታጣ አድርገዋል። ይህም የካይሮ የረጅም ጊዜ “ኢትዮጵያን የመዝጋት” ስትራቴጂ አካል እንደነበር ግልጽ ነው። የካይሮ መጥረቢያ እና አሁናዊው የጥፋት መንገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት የመጥረቢያ ተምሳሌታዊ ማብራሪያ፣ ሕገ ወጡ ሕወሃትን እንደ መጥረቢያ ብረት፤ ሻዕቢያን ደግሞ እንደ መጥረቢያ ዛቢያ ያስቀመጡ ሲሆን፤ መጥረቢያውን የሚያዘውና የሚወረውረው ሌላ ሶስተኛ አካል መኖሩንም ተናግረዋል። እንደሚታወቀው መጥረቢያ አንድን ነገር የመቁረጥና የማፍረስ ስራ ለማከናወን የሶስት አካላት ቅንጅት ያስፈልገዋል፦ ወርዋሪው (እጁ)፣ ዛቢያው (መያዣው) እና ብረቱ (ቁራጩ)። በዚህ ተምሳሌት ውስጥ ወርዋሪው ወይም መጥረቢያውን ጨብጦ ስራ ላይ የሚያውለው አካል ግብፅ ናት። ወርዋሪው ሁልጊዜም ከበስተጀርባ ሆኖ ስትራቴጂ ይነድፋል፣ ፋይናንስና ወታደራዊ ድጋፍ ያቀርባል፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሽፋን ይሰጣል። በሌላ በኩል የመጥረቢያ ብረት ያለ ዛቢያው (መያዣው) ኃይል አግኝቶ ማረፍ አይችልም፤ ዛቢያውም ያለ ወርዋሪው እጅ መንቀሳቀስ አይችልም። በዚህ ሂደት ሻዕቢያ (እንደ ዛቢያ) በቀጣናው ውስጥ የካይሮን ፍላጎት ለማስፈጸም የመያዣነት ሚና ይጫወታል። ቀጣናውን ለማተራመስ በሞመከር የካይሮን ስትራቴጂካዊ ፍላጎት ለማሳካት መንገድ ይከፍታል። ህገ-ወጡ ህወሓት ደግሞ እንደ መጥረቢያ ብረት በሀገር ውስጥ ሆኖ የሀገሪቱን መዋቅር፣ የህዝቦችን አንድነት እና ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ጥቅም ለመሸርሸር የሚሰራ ተላላኪ መሳሪያ ነው። በዚህ የሴራ ትስስር አሁን ላይ ኢትዮጵያ በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት ማደናቀፍ ዋነኛ ዓላማው አድርጎም እየሰራ ይገኛል። ግብፅ “የቀይ ባሕርና የኤደን ባሕረ-ሰላጤ የባሕር ወሰን ያላቸው ሀገራት ብቻ ናቸው በውሃው ላይ መወሰን ያለባቸው” የሚል መርህ በማንሳት፣ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትንና በቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኘውን ትልቁን ኢኮኖሚ (ኢትዮጵያን) ያገለለ ህገ-ወጥ ስብስብ ለመፍጠር እየሰራች ነው። በተጨማሪም በቅርቡ ከሶማሊያና ከሌሎች የአካባቢው ሀገራት ጋር የተደረጉ የውትድርናና የደህንነት ስምምነቶች፣ የሶማሊያን ሰላም ለማስጠበቅ ሳይሆን ቀጣናውን ለማተራመስና ወታደራዊ ስጋት ለመፍጠር የተቃኙ ናቸው። ይህ ሁሉ አካሄድ ዋነኛ ዓላማው ቀጣናውን የውክልና ጦርነት ማዕከል በማድረግና ኢትዮጵያ ወደ ባሕር እንዳትቀርብ ሆነ ተብሎ የተሰላ ሴራ ነው። ከቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ እስከ ዛሬው የቀይ ባሕር ሴራዎች ድረስ የተዘረጉት መረቦችም ይህንኑ እውነት ያሳያሉ። የካይሮ መጥረቢያዎችን ያዶለዶመው የመደመር መንግሥት ጥንካሬ ግብጽ እያከናወነችው ባለው አሁናዊ ሴራ ውስጥ የካይሮ ስትራቴጂስቶች የሳቱት ትልቅ እውነታ አለ። የግብጽ የሴራ መጥረቢያዎች ለመቁረጥ የሚሞክሩት በፈተናዎች የማትበገረውን እና እንደ ወርቅ በእሳት ውስጥ ተፈትና ያለፈችውን ኢትዮጵያን መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በታሪኳ የውጭ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎችን አሸንፎ መውጣት እንግዳ የሆነባት ሀገር አይደለችም። ባለፉት ክፍለ ዘመናት በወረራ፣ በውስጥ አለመረጋጋትና በጂኦፖለቲካዊ ከበባዎች ውስጥ አልፋ የጸናች ሀገር ናት። ወርቅ በእሳት ውስጥ ሲያልፍ ቆሻሻው ተወግዶ ይበልጥ እንደሚበራ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በተጋረጡባት የህልውና ፈተናዎች ሁሉ አልፋ ይበልጥ እየጠነከረችና እየተደራጀች መምጣቷ የታሪክ እውነታ ነው። አሁን ባለንበት ዘመን ደግሞ ይህ ጥንካሬዋ ይበልጥ ጎልብቷል። የመደመር መንግሥት ቁልፍ ፍልስፍና እና እየተገበራቸው ያሉ እርምጃዎች የካይሮን የረጅም ጊዜ የእጅ አዙር ጦርነትና ሴራዎችን ከንቱ ያደረገ ነው። የመደመር መንግሥት የውጭ ጫናዎችንና ሴራዎችን ለመመከት የመጀመሪያው ምሽግ የውስጥ አቅምን ማጠናከር መሆኑን በመገንዘብ፣ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለፍፃሜ ማብቃትና ግዙፍ የግብርና፣ የአረንጓዴ አሻራ እና የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን እውን አድርጓል። ይህም ግብፅ ኢትዮጵያን በልማት እንዳትበለፅግ ለማድረግ ያቀደችውን ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ አክሽፎታል። ካይሮ ኢትዮጵያን በጂኦፖለቲካዊ ከበባ ለማዳከምና በውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የነደፈችው የረጅም ጊዜ የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት ባስመዘገባቸው የልማትና የዲፕሎማሲ ድሎች ምክንያት ሙሉ በሙሉ ተደርምሷል። ይህ የጠላት ካምፕ መደርመስና የኪሳራ ስሌት ደግሞ በካይሮ ስትራቴጂስቶችና በውስጥ ተላላኪዎቻቸው (ባንዳዎች) ዘንድ ታላቅ ድንጋጤንና ተስፋ የመቁረጥ እሪታን ፈጥሯል። በመሆኑም የተበተነው የጠላት ካምፕና የተበሳጩት ባንዳዎች ብቸኛ አማራጭ አድርገው የያዙት በሳይበርና በሚዲያ ምህዳር የሃሰት መረጃዎችን ማንደድና የፕሮፓጋንዳ ማዕበል መፍጠር ቢሆንም፣ ይህም የተስፋ መቁረጥ ድምፅ ብክለት እንጂ የኢትዮጵያን የጽናት ጉዞ የሚያስተጓጉል አይሆንም። በሌላ በኩል ግብፅ “የቀይ ባሕር ሀገራት ጥምረት” በሚል ስም ቀጣናውን ለማተራመስና እርስ በርስ ጥርጣሬ ለመፍጠር የምታደርገውን የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት የጋራ እድገትና የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በማስቀደም በዲፕሎማሲው መስክ እየመከተው ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ምክክር የጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ በጋራ እንዲወስኑ በማድርግም የካይሮ ስትራቴጂስቶች በኢትዮጵያ የውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የጠነሰሱትን ሴራ ከንቱ አድርጎታል። በአጠቃላይ ታሪክ እንደሚነግረንና የወቅቱ እውነታ እንደሚመሰክረው፣ የግብፅ የሴራ መጥረቢያዎች በፈተናዎች እሳት ተፈትና ባላለፈች ደካማ ሀገር ላይ ያረፉ አይደሉም። ለመቁረጥ የሞከሩት በጽናት፣ በህዝቦቿ መስዋዕትነትና በፅኑ ታሪካዊ መሰረት ላይ የቆመችውን ኢትዮጵያን ነው። አሁን ላይ በመደመር መንግሥት መሪነት እየተገነባ ያለው የውስጥ አቅም፣ የልማት ስኬትና በራስ መተማመን የካይሮን የረጅም ጊዜ የከበባ ሴራ ሙሉ በሙሉ ወድቅ ማድረጉን ቀጥሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ሁሉ አሸንፎ ማለፍ የሰርክ ተግባሯ እንደመሆኑ መጠን፣ የዛሬውንም የጂኦፖለቲካ ውጥረትና የሴራ መረብ በጽናት አልፋ የቀጣናው የልማትና የሰላም ማዕከል ሆና መቀጠሏ የማይቀየር እውነት ነው።
ምክክሩ ኢትዮጵያን ማጽናት የሚያስችል ትልቅ መሰረት እየጣለ ይገኛል-ተመካካሪዎች
Aug 19, 2026 152
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ) ፦ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያን በጠንካራ የተግባቦት ዓለት ላይ ለማጽናት ትልቅ መሰረት እየጣለ እንደሚገኝ ተመካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ለዘመናት በኢትዮጵያ የዘለቁ አለመግባባቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት፣ኢትዮጵያዊያን ካለፈው ኋላቀር እሳቤ በመላቀቅ ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እያደረጉ ይገኛል። ይህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 4 ሺህ ኢትዮጵያውያን እየተመካከሩበት በሚገኘው በዚህ ጉባኤ፣የተመካካሪዎች ሀሳብ በነጻነት የሚንሸራሸርበት ነጻ እና ዴሞክራሲያዊ አውድ ተፈጥሯል። በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሄደ ያለው ይህ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያን በጠንካራ የተግባቦት ዓለት ላይ ለማጽናት ትልቅ መሰረት የሚጥል መሆኑን ከፖለቲካ ፓርቲዎች የተወከሉ ተመካካሪዎች ለኢዜአ ገልጸዋል። ከተመካካሪዎች መካከል የአፋር ነጻ አውጪ ግንባርን ወክለው የመጡት ሀጂ እስማኤል መሀመድ እንዳሉት፣የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በማካተት በሰለጠነ አግባብ እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ ተመካካሪዎች ሃሳባቸውን በነጻነት የሚያንሸራሽሩበት በመሆኑ ዘላቂ ሰላም እና ሀገራዊ መግባባትን ለማስፈን ትልቅ ዕድል እየፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተወክለው የሚወያዩበት ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ የሀገሪቱን የልማት እና የዴሞክራሲ ጉዞ ለማቀላጠፍም ወሳኝ ምዕራፍ እንደሚከፍት ተናግረዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ የሲዳማ አርነት ንቅናቄን ወክለው በመሳተፍ ላይ ያሉት ደምሴ ስኳሬ ፣ የምክክር ሂደቱ ከመነሻው ጀምሮ ግልጽነትና አሳታፊነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሂደቱ ከታች ጀምሮ የተለያዩ ሀሳቦችን በማብሰልና በማዋሃድ ወደ ላቀ የጋራ ሀገራዊ መግባባት የሚያደርስ እና ይህም የሂደቱን የሰለጠነ አካሄድ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ምክክሩ ለሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የመላው ተመካካሪዎች ድምፅ በነጻነት የተደመጠበት ሁሉን አቀፍ ጉባኤ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን በመወከል በመሳተፍ ላይ ያሉት ተመካካሪ ነጻነት ጣሰው ናቸው።   ተመካካሪዎች እርስ በርሳቸው እንዲተዋወቁና ጠንካራ አዎንታዊ ግንኙነት እንዲፈጥሩ ሰፊ ዕድል በመፍጠር ሂደት ውስጥ ልዩ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግረዋል። መድረኩ ኢትዮጵያን የሚያሻግሩ ገንቢ ሀሳቦች እየተነሱበት በመሆኑ የመደማመጥ እና የጋራ መግባባት ባህልን ለማጠናከር ትልቅ አጋጣሚ መፈጠሩንም አንስተዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች መካተታቸው የተሻለች ሀገር በጋራ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል።
ከምክክር ጉባዔው ለፖለቲካዊ አለመግባባቶች መፍትሔ የሚሆኑ ምክረ ሃሳቦችን እንጠብቃለን - የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች
Aug 19, 2026 156
አዳማ፤ ነሐሴ 13/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ለፖለቲካዊ አለመግባባቶች መፍትሔ የሚሆኑ ምክረ ሃሳቦችን ይሰጣል የሚል ትልቅ እምነት እንዳላቸው የአዳማ ከተማ አባ ገዳ እና የሃይማኖት አባት ተናገሩ። ከሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡት የአዳማ ከተማ አባ ገዳ እና የሃይማኖት አባት፣ አካታችነቱና አሳታፊነቱ ጎልቶ የታየው የሀገራዊ ምክክር ጉባዔው በፖለቲካዊ አለመግባባቶች ላይ ዘላቂ መፍትሔና ምክረ ሃሳቦችን ያመጣል የሚል ትልቅ እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። በአዳማ ከተማ የቦኩ ክፍለ ከተማ አባገዳ ተሾመ ስማ እንደገለፁት ሀገራዊ ምክክሩ በዘመናት ውስጥ ሀገራችን ያገኘችው ታሪካዊ ድል ነው ብለዋል። ተመካካሪዎች ህዝቡን ወክለው ለኢትዮጵያ የተሻለ መፍትሔ ለማስቀመጥ እየመከሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ በሀገሪቱ በህዝቦች መካከል የቆዩ ቅሬታዎችንና ቁርሾዎችን በመሻር ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ትልቅ መሰረት እንደሚጥል ተስፋ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። መንግሥትም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር ጉባዔውን ምክረ ሀሳቦች በማክበርና ወደ ተግባር በመለወጥ ረገድ መተባበር እንዳለባቸው ገልጸዋል። ሀገራችንና ህዝባችን ይህንን እድል በማግኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን የገለጹት አባገዳው፤ ከምክክር ጉባዔው ትልቅ ውጤት እንደሚጠብቁም አክለው ተናግረዋል። የአዳማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አባል ሼህ አብዱልቃድር አህመድ እንደገለፁት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የነበሩ ቁርሾዎችን በሁለንተናዊ መልኩ እንደሚፈታ ተስፋ አድርገዋል። በተለይም በሀገሪቱ የነበሩትን የፖለቲካ አለመግባባቶች ለመቅረፍ ብቸኛው መፍትሔ ምክክር መሆኑን ገልጸዋል። በምክክሩ ጥሩ መፍትሔ ይመጣል የሚል ተስፋ እንዳላቸው የገለጹት ሼህ አብዱልቃድር፤ ለተፈጻሚነቱ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንደሚወጡም ተናግረዋል። ምሁራን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የቀድሞ ታጣቂዎች፣ የሃይማኖት ተወካዮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የፀጥታ አካላት እንዲሁም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት የምክክር ጉባዔ በመሆኑን ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ አጀንዳ ከማሰባሰብ ጀምሮ ሁሉንም ያማከለ፣ አሳታፊና አካታች እንደነበር የገለጹት ሼህ አብዱልቃድር፤ ሂደቱ ለሀገራችን ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያመጣ ሙሉ እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
በምክክር ጉባኤው ምክረ ሀሳቦች የተጠናቀረው የመጨረሻ ሰነድ ነገ ለአራት ሺህ ተመካካሪዎች በጋራ ይቀርባል-ኮሚሽኑ
Aug 19, 2026 205
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በቀረቡ ምክረ ሀሳቦች ላይ የተጠናቀረው የመጨረሻ ሰነድ ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ለአራት ሺህ ተመካካሪዎች በጋራ እንደሚቀርብ አስታወቀ። የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገብረሥላሴ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን አሁናዊ ሁኔታ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ ከስምንቱም ቡድኖች የቀረበውን ምክረ ሀሳብ ለማጣጣም የተቋቋመው 120 አባላት ያሉት አጠናቃሪ ቡድን በጥንቃቄ ሲሰራ ቆይቶ እስከ ትናንት ምሽት ድረስ አንድ ወጥ የሆነ ሰነድ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል። እንደ ኮሚሽነሯ ገለጻ፣ የተዘጋጀው ሰነድ ዛሬ ጠዋት ለየስምንቱ ቡድኖች የቀረበ ሲሆን፣ ቡድኖቹ ሰነዱን አዳምጠው የመጨረሻ ግብዓትና አስተያየት እየሰጡ እንደሚገኝ አመልክተዋል። አጠናቃሪ ቡድኑ ዛሬ ማምሻውን እነዚህን የተሰበሰቡ አስተያየቶች በማካተት የመጨረሻውን ሰነድ አጠናቆ እንደሚያዘጋጅ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የተጠናቀረው የመጨረሻ ሰነድ ለአራት ሺህ የጉባኤው ተሳታፊዎች በጋራ የሚቀርብ ሲሆን፣ይህም ሂደቱ ትልቅ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የሚያመላክት ነው ብለዋል። ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ህዝቡ አንዳንዶች የሚያሰራጩትን የተዛባ መረጃ በመስማት እንዳይወዛገብ እና ለትክክለኛ መረጃዎች የኮሚሽኑን መግለጫዎች ብቻ እንዲከታተል አሳስበዋል።
ምክክሩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የሀገሪቱ መፃኢ እድል ብሩህ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን-ነዋሪዎች
Aug 19, 2026 169
ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የሀገሪቱ መፃኢ እድል ብሩህ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የቦንጋና ታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ለዘመናት ለቆዩ አለመግባባቶች መንስኤ የሆኑ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ በጋራ መክሮ ለመፍታት እንደሚያስችል የታመነበት የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል። አካታችና አሳታፊነቱ ጎልቶ የታየበት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በታሪክ የታየውን ልዩነት በሰለጠነ መንገድ በመወያየት የሚሰጣቸው የመፍትሔ ሀሳቦች ሀገራዊ መግባባትን እንደሚፈጥሩ በህዝቦች ዘንድ ተስፋ ተጥሎበታል። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋና የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ሀገራዊ ምክክሩ የነበሩ አለመግባባቶችን በውይይትና በምክክር በመፍታት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። ነዋሪዎቹ አክለውም፤ ምክክሩ ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የሀገሪቱ መፃኢ እድል ብሩህ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል። የቦንጋ ከተማ ነዋሪው አቶ ታሪኩ ታዬ፤ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር ታሪካዊና ለረጅም ዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የሀገራችንን መፃኢ እድል የሚወስን መሆኑን ተናግረዋል። ከአራቱም የሀገሪቱ አቅጣጫዎች የተወከሉ ኢትዮጵያውያን በጋራ ቁጭ ብለው በጠረጴዛ ዙሪያ መምከራቸው በሀገራቸው ጉዳይ ያገባኛል የሚል እምነት እንዲኖራቸውና የመፍትሔው አካል መሆን የሚያስችላቸው ትልቅ እድል እንደሆነም ገልጸዋል። እንደ አቶ ታሪኩ ገለጻ፤ ምክክሩ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለአፍሪካ ሰላምና አንድነት ፋና ወጊ ሀገር ሆና ሳለች የውስጥ ችግሮቿን በውይይትና በምክክር መፍታት ተስኗት የቆየችበትን ታሪክ በማደስ ወደ አዲስ ምዕራፍ የምትሸጋገርበት ትልቅ ዕድል ነው። የምክክር መድረኩ ለዘመናት ሳይፈቱ የቆዩ ውስብስብ ችግሮችን ተወያይቶ ለመፍታትና ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር የሀገርን ሰላምና እድገት እንደሚያጠናክር ተስፋቸውን የገለጹት ሌላኛው የቦንጋ ከተማ ነዋሪ አቶ ደመረ ጌታሁን ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያውያን በተወካያቸው አማካይነት የተሳተፉበት መሆኑ ለሀገር ሰላምና ብልፅግና በአንድነት መቆም የሚያስችል ውጤት እንደሚያመጣ እምነታቸው መሆኑን ነው የገለጹት። በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ነዋሪው አቶ አብርሃም አሳሮ በበኩላቸው፤ ምክክሩ እየተካሄደባቸው ባሉት አጀንዳዎች የሚደረሱ ውጤቶች በኢትዮጵያ የነበሩ በርካታ አለመግባባቶች፣ መቃቃሮችና አለመደማመጦችን በዘላቂነት የሚፈቱ እንደሚሆኑ እምነታቸው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ እየተካሄደ መሆኑ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄዎችና ሐሳቦች በተወካዮቻቸው በኩል እንዲነሱ ያስቻለ በመሆኑ አንድነትንና አብሮነትን በማጠናከር ሀገራዊ መግባባትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ምክክሩ እኔ የሚለውን ነጠላ ትርክት እኛ በሚለው የወል ትርክት በመተካት ሀገራዊ እይታን ያጎላል ያሉት አቶ አብርሃም፤ ይህም ኢትዮጵያውያን ለሀገር ሰላምና ልማት በጋራ መቆም የሚያስችላቸው ወርቃማ እድል መሆኑን ጠቁመዋል። ሀገራዊ ምክክሩ አለመግባባቶችንና ችግሮችን ከምንጫቸው በሰለጠነ መንገድ በውይይት በመፍታት በአብሮነትና በአንድነት ወደፊት ለመራመድ ያስችለናል ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ዘሪሁን ለማ ናቸው። ኢትዮጵያ የረጅም ዘመናት ታሪክና ችግሮቿን በውስጥ አቅም መፍታት የሚያስችሏት የበርካታ ሀገር በቀል እውቀቶች ባለቤት መሆኗን የገለጹት አቶ ዘሪሁን፤ ምክክሩ በዚህ ላይ የተመሰረተና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ትልቅ ተስፋን የያዘ አዲስ ምዕራፍ ነው ብለዋል።
ማህበራዊ
በ2019 ትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ዝግጅት እየተደረገ ነው
Aug 19, 2026 113
ደሴ፤ ነሐሴ 13/2018(ኢዜአ)፡-በደሴ ከተማ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የከተማው ትምህርት መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው የ2019 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ አካሂዷል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፍቅር አበበ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በትምህርት ዘመኑ ከ77 ሺህ በላይ ተማሪዎችን መዝግቦ ለማስተማር እንቅስቃሴ ተጀምሯል።   ለዚህም አመራሩ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት በየደረጃው የንቅናቄ መድረኮችን እያካሄደ ይገኛል ብለዋል። ከነገ ጀምሮም በተመረጡ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምዝገባ እንደሚጀምር የተናገሩት ኃላፊው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምዝገባውን በማጠናቀቅ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም የመማር ማስተማር ሥራው በይፋ ይጀመራል ብለዋል። በትምህርት ዘመኑ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻልና ባለፉት ዓመታት የተጀመረውን የተማሪዎች ምገባ በማስፋፋት የትምህርት ጥራቱን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ለዚህም 20 አዳዲስ መማሪያ ክፍሎች ተገንብተው ለመማር ማስተማር ስራ ዝግጁ ከመሆናቸው ባለፈ፣ ነባር 128 መማሪያ ክፍሎች ደረጃቸው ተሻሽሎ ተዘጋጅተዋል ብለዋል። የመምህር አካለ ወልድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አንዳርጌ አፍሬ በበኩላቸው፤ በ2019 ትምህርት ዘመን ከሁለት ሺህ በላይ ተማሪዎችን መዝግቦ ለማስተማር ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። ምዝገባውን በአምስት ቀናት ውስጥ በማጠናቀቅ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም የመማር ማስተማሩን ስራ ለመጀመር ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የ2019 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራውን ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የተናገሩት ደግሞ የሰኞ ገበያ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ረህመት ይመር ናቸው። ለዚህም ግብዓት በማሟላት፣ ትምህርት ቤቱን የማሳመርና የማስዋብ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። በመድረኩ የከተማ፣ የክፍለ ከተማና የትምህርት ቤቶች አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።  
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ከ120 ሺህ ለሚበልጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ነጻ የሕክምና አገልግሎት ሰጠ
Aug 19, 2026 96
ዲላ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፡-የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከ120 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ነጻ የሕክምና አገልግሎት መስጠቱን አስታወቀ። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታሉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ትዝአለኝ ተስፋዬ ለኢዜአ እንደገለጹት ሆስፒታሉ በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ነጻ የሕክም እየሰጠ ነው።   በተያዘው ክረምትም የዲላ ማረሚያ ተቋምን ጨምሮ በከተማዋ በአራት ጊዜያዊ ጣቢያዎች ለህብረተሰቡ የነጻ የሕክም አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ገልጸዋል። የሕክምና አገልግሎቱ የሳንባ ነቀርሳና የስነ አዕምሮ ጤና ዘርፎችን ጨምሮ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ልየታ፣ ሕክምናና የመድሃኒት አቅርቦትን ያካተተ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም ከ120ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው፣ በበጎ ፍቃድ የሕክምና አገልግሎቱ ስፔሻሊስት ሃኪሞችን ጨምሮ 100 የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች መሳተፋቸውን ተናግረዋል።   ከነጻ የሕክምና አገልግሎቱ በተጨማሪ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር የደም ልገሳና የአረጋዊያን ድጋፍ መርሀግብሮች መከናወናቸውን ጠቁመው፣ የተሰጠው ነጻ የሕክምና አገልግሎት የሆስፒታሉን ጫና አቃሎታል ብለዋል። በቀጣይም ነጻ የሕክምና አገልግሎቱ ከከተማው ወጭ በጌዴኦ ዞን እና አጎራባች ወረዳዎች እንደሚሰጥም ተናግረዋል። በማረሚያ ተቋሙ የተሰጠው ነጻ የሕክምና አገልግሎት የታራሚዎችን ጤና ከመጠበቅ ባሻገር ትልቅ የሞራል ድጋፍ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የዲላ ማረሚያ ተቋም አዛዥ ኢንስፔክተር ትዕግስት ሮቤ ናቸው።   የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራሮች እና የጤና ባለሙያዎች ላደረጉት ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ነጻ የሕክምና አገልግሎት ካገኙት ነዋሪዎች ውስጥ አቶ ታፈሰ ፎላ በነጻ ሕክምናው ሙሉ የጤና ምርመራ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።   በምርመራውም የወባ በሽታ እንዳለባቸው ምልከት በመታየቱ በሆስፒታሉ የመድሃኒት አገልገሎትም ማግኝታቸውን ተናግረዋል። ነጻ የሕክምና አገልግሎቱ ሙሉ የጤና ሁኔታቸውን ለማወቅ እንዳስቻላቸው የተናገሩት ድግሞ ወይዘሮ እቴነሽ ወርቁ ናቸው። በተለይ የዓይንና የስነ አዕምሮ ምርመራ በማድረጋቸው መደሰታቸውን ገልጸው ለተሰጣቸው ነጻ የምርምራ አገልግሎት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።    
የሻደይ በዓል የሀገር ባህል አልባሳትና ጌጣጌጥ ገበያን እያነቃቃ ነው - የባህል ልብስ ሰሪና አቅራቢዎች
Aug 19, 2026 93
ሰቆጣ፤ ነሃሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በየዓመቱ የሚከበረው የሻደይ በዓል የአካባቢውን ባህልና ትውፊት ከማስተዋወቅ ባለፈ የሀገር ባህል አልባሳትና የጌጣጌጥ ገበያን እያነቃቃ እንደሚገኝ ነጋዴዎች ገለጹ። የልጃገረዶች ጨዋታና የውበት መግለጫ፣ የባህል አልባሳትና የጌጣጌጥ ድምቀት የሆነው የሻደይ፣ አሸንድዬና ሶለል በዓል የዓመቱ ማጠቃለያና የአዲሱ ተስፋ ማብሰሪያ በመሆን በተለያዩ አካባቢዎች በደመቀ ሥነ-ሥርዓት ይከበራል። የሴቶችን ማህበራዊና ባህላዊ እሴት ከማጎልበት ባለፈ የአገር ባህል አልባሳት፣ የጌጣጌጥና የቱሪዝም እንቅስቃሴን የሚያነቃቃው የሻደይ፣ አሸንድዬና ሶለል በዓል በየዓመቱ ከነሐሴ 15 ቀን ጀምሮ በስፋት ይከበራል።   የሻደይ በዓል ሴቶች በአቅማቸው ልክ የባህል አልባሳትንና ጌጣጌጥ በመግዛት አጊጠውና ተውበው ለማክበር ዕለቱን በናፍቆት የሚጠብቁት ዓመታዊ በዓል ነው። በሰቆጣ ከተማ የባህል አልባሳት ነጋዴ የሆኑት ወይዘሮ አበበች ወርቁ፤ ለበዓሉ የዋግ ባህል መገለጫ የሆኑ አልባሳትን አዘጋጅተው እየሸጡ መሆኑን ገልፀዋል። በሁሉም የዕድሜ ክልል ለሚገኙ የአካባቢው ማሕበረሰብ የባህል አልባሳትን በማዘጋጀት ይዘው መቅረባቸውን ጠቁመው፣ በዓሉ ሲደርስ ገበያው የተሻለ እንደሚሆን ተናግረዋል።   ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ መዝገቡ ሚሰነ በበኩላቸው፤ ህብረተሰቡ ለባህል አልባሳት እየሰጠ ያለው ትኩረት በገበያው ላይ ትልቅ ለውጥ እያመጣ በመሆኑ በዘርፉ ለመሰማራት አስችሎኛል ነው ያሉት ። የአካባቢው ማህበረሰብም ከጊዜ ወደ ጊዜ የባሕል ልብሱን ከመሸመን ጀምሮ በጥልፍና በስፌት ሥራ በመሰማራት ተጠቃሚነቱን እያሳደገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በመጪው ነሐሴ 15 ጀምሮ ለሚከበረው የሻደይ በዓል የሚሆን በቂ የባህል አልባሳትን አዘጋጅተው ማቅረባቸውን ያመለከቱት አቶ መዝገቡ፣ ህብረተሰቡም ገበያዉን እየተጠቀመበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።   በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ይርጋ ማርዬ እንዳሉት፤ የዘንድሮው የሻደይ በዓል "ሻደይን እናከብራለን፤ እሴቶቻችንን እንጠብቃለን" በሚል መሪ ቃል ይከበራል። መምሪያው በዓሉ ባህላዊ ክዋኔውንና እሴቱን በጠበቀ መልኩ ለትውልድ እንዲተላለፍ እየሰራ ሲሆን፣ ለዚህም የባህል አልባሳት ሰሪዎች፣ በጥልፍ ሥራ የተሰማሩና አቅራቢዎች ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳላቸው አስገንዝበዋል። ከነሐሴ 15 ጀምሮ ለሚከበረው የሻደይ በዓል እሴቱንና ትውፊቱን የጠበቀ የባህል አልባሳትና ጌጣጌጥ እንዲቀርብ በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱንም አስረድተዋል። በዓሉ በየአካባቢው የተለያየ መጠሪያ ስም ያለው ሲሆን፣ ሻደይ በዋግ ኽምራ፣ አሸንድዬ በላስታ/ወሎ፣ ሶለል ደግሞ በራያ ተብሎ እንደሚሰየም ይታወቃል።
ኢኮኖሚ
በይርጋዓለም ከተማ የሌማት ትሩፋት መርሀግብር የዶሮ አርቢዎችን ኢኮኖሚያዊ አቅምን እያሳደገ ነው
Aug 19, 2026 111
ይርጋለም፤ ነሀሴ 13/2018 (ኢዜአ)፡-በይርጋዓለም ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዶሮ እርባታ ሥራ የተሰማሩ ማህበራት ከእንቁላል ምርታቸው ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ገለጹ። በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ይርጋዓለም ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ማህበራት እንደገለጹት፣ የተሰማሩበት የዶሮ እርባታ ሥራ የእንቁላል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ አቅማቸውን እያሳደገው ነው። ከእንቁላል ሽያጭ በሚያገኙት ገቢ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱንም ለኢዜአ ገልጸዋል።   ‎በከተማው የጌዶሴይ ዶሮ እርባታ ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ከተማ ካቢሶ ሥራውን በ1 ሺህ የእንቁላል ጣይ ዶሮዎች እንደጀመሩ አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ያሏቸው የዶሮዎች ቁጥር 4 ሺህ መድረሱን ተናግረዋል። ከእነዚህም በቀን ከ3 ሺህ 700 በላይ እንቁላል እንደሚሰበስቡና ከሽያጩም የተሻለ ገቢ እያገኙ መሆናችውን አስረድተዋል።   ከእንቁላል ምርት ባለፈ የአንድ ቀን ጫጩቶችን በማስመጣትና አሳድገው በ48 ቀናቸው ለተጠቃሚዎች በማስረከብ ተጨማሪ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ከመንግስት የመስሪያ ቦታ፣ የስልጠናና ሌሎች ድጋፎችን እያገኙ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።   የደረሰና ቤተሰቡ የዶሮ እርባታ ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረሰ አሰፋ በበኩላቸው "የዶሮ እርባታ ሥራ አስፈላጊ መኖና ሕክምናን ከማሟላት ባለፈ በጥንቃቄ መስራት ከተቻለ ትርፋማ ያደርጋል" ብለዋል። በአንድ ሺህ የእንቁላል ጣይ ዶሮዎች የጀመሩትን ሥራ አስፋፍተው በአሁኑ ወቅት ከ10ሺህ በላይ ዶሮዎች እንዳሏቸው ገልፀዋል፡፡ በቀን ከ9 ሺህ በላይ እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ደረሰ፣ በስራቸው ለሌሎቸም የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ነው የተናገሩት ከመንግስት ነጻ የዶሮ ክትባቶችን ጨምሮ የሙያና የተለያየ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም ገልፀዋል፡፡   የሲዳማ ክልል እንስሳት ሀብት ልማት ቢሮ ምክትልና የዝርያ ማሻሻልና መኖ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አደገ አለሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው በክልሉ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የዶሮ ልማት ሥራ ትልቅ እመርታ ማሳየቱን ገልጸዋል፡፡ የዶሮ ሀብት ልማት በየቤታቸው የተወሰኑ ዶሮዎችን የሚያረቡ አርሶ አደሮች፣ በማህበር ተደራጅተው የሚሰሩ ዜጎችን እንዲሁም በግል የሚያለሙ ባለሀብቶችን ተጠቃሚ አድርጓል ብለዋል። በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት እና ዶሮ ፈላጊዎች የዶሮ አቅርቦት፣ የሙያ እገዛና ሌሎች የድጋፍና ክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ኃላፊው አደገ (ዶ/ር) ጠቁመዋል፡፡ እንደእሳቸው ገለጻ ከአምስት ዓመት በፊት በክልሉ በዓመት ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በታች የነበረውን የዶሮ ሥርጭት በአሁኑ ወቅት 20 ሚሊዮን ለማድረስ ተችሏል። በተያዘው 2019 በጀት ዓመትም 24 ሚሊዮን ዶሮዎችን ለማሰራጨት ማታቀዱን ጠቁመዋል፡፡    
በድሬደዋ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት የተሰማሩ አልሚዎችን በመደገፍ የኮንፍረንስ ቱሪዝምን ማሳደግ ተችሏል
Aug 19, 2026 72
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 13/2018(ኢዜአ)፦ በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት የተሰማሩ አልሚዎችን በመደገፍ የኮንፍረንስ ቱሪዝምን ማሳደግ መቻሉን የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ ገለጹ። የከተማ አስተዳደሩ አመራር አካላት በሆቴል ኢንቨስትመንት ለመሰማራት ፈቃድ ወስደው ግንባታ ላይ የሚገኙ ባለኮከብ ሆቴሎችን የመስክ ጉብኝት አድርገዋል። ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ አስተዳደሩ የከተማዋን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት የቀየሰው የአሰራርና የህግ ማእቀፍ በርካታ አልሚዎችን ወደ ስራ ማስገባት አስችሏል። ለዚህም የመሠረተ ልማት፣ የመሬት አቅርቦት፣ የውሃ፣ የኤሌክትሪክ፣ የፋይናንስ እና ሌሎች ድጋፎችን ከመስጠት አኳያ ከተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ይህም በተለይም በሆቴሎች ዘርፍ ፈቃድ ወስደው በግንባታ ላይ የነበሩ አልሚዎች ስራቸውን አጠናቀው ወደ አገልግሎት በመግባት የቱሪዝሙን እንቅስቃሴ እያሳደጉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለአብነትም በበጀት አመቱ በግንባታ ላይ የነበሩ አምስት ሆቴሎች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን አንስተዋል። ይህም ከተማዋን የቱሪዝም ኮንፍረንሰ ማእከል ለማድረግ የተጀመረውን ጥረት ለማሳካትና የቱሪስቶችን ቆይታ ለማራዘም ማገዙን ገልጸዋል ። የዛሬው ጉብኝትም አስተዳደሩ በሆቴል አገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶችን ለማበረታታት ያለመ ነው ብለዋል። እንዲሁም በግንባታ ላይ ያሉ ሆቴሎችን በማበረታታት በፍጥነትና በጥራት ወደ አገልግሎት ለማስገባት አቅጣጫ ለማስቀመጥ መሆኑን ጠቅሰዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ አስተዳደሩ ተፈጥሮአዊና ታሪካዊ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማት የዘርፉን ጠቀሜታ ለማጉላት እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም መስህቦቹን ለጎብኚዎች አመቺ የማድረግና ከከተማዋ ኮሪደር ልማት ጋር ተሰናስሎ እንዲሄድ መደረጉን ገልጸዋል። በከተማዋ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶችን ፍሰትና የቆይታ ጊዜ ለማራዘም የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ማስፋፋት ላይ ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመዋል። በዚህም በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ700 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ እና ከ15 ሺህ በላይ ቱሪስቶች መስህቦቹን መጎብኘታቸውን አስረድተዋል። የከተማዋ የቱሪዝም ልማትም የስራ እድልን ለማስፋትና የከተማውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ከፍ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። በተያዘው በጀት አመትም በቱሪዝም ዘርፍ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በግንባታ ላይ ከሚገኙ ባለኮኮብ ሆቴሎች ባለቤት አቶ ሱራፌል ሲሳይ በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ ለዘርፉ የሚያደርገው ድጋፍና ክትትል ስራቸውን ለማቀላጠፍ እያገዛቸው መሆኑን ጠቅሰዋል። በግባታ ላይ የሚገኘው ሆቴልም ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰትና ለወጣቶች የስራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል።      
በአማራ ክልል የአፈር ለምነትን የሚያሻሽል የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል
Aug 19, 2026 85
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በበጀት ዓመቱ የአፈር ለምነትን የሚያሻሽል 86 ሚሊዮን ሜትር ኩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ ወደተግባር መገባቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የአፈር ለምነት ባለሙያ አቶ አምሳሉ አድማስ ለኢዜአ እንደገለጹት በአሲድ የተጠቃ አፈር ለምነትን ለመመለስና የሰብል ምርታማትን ለማሳደግ የተፈጥሮ ማዳበሪያን አዘጋጅቶ መጠቀም ጠቀሜታው የጎላ ነው።   ለዚህም በበጀት ዓመቱ ከ3 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚበልጡ አርሶ አደሮችን በተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት በማሳተፍ 86 ሚሊዮን ሜትር ኩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ግብ ተይዞ ወደተግባር ተገብቷል። ከቅጠላቅጠሎች፣ ከተረፈ ምርት፣ ከከብቶች እዳሪ፣ ከአመድና ለኮምፖስት ዝግጅት ጠቃሚ ከሆኑ ሌሎች ንጥረ ነገሮች ጥራቱን ጠብቆ እንዲዘጋጅ ለአርሶ አደሩ ሙያዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑንም ገልጸዋል። የተፈጥሮ ማዳበሪያ ሳይንሳዊ ሂደቱን ጠብቆ ከተዘጋጀ የአፈር ቅንጣትና ለምነት እንዲሻሻል፣ የሰብል ምርታማነት እንዲጨምር፣ አፈር በውስጡ ውሃን ለረጅም ጊዜ እንዲቋጥር የጎላ ጠቀሜታው እንዳለውም አመልክተዋል። በበጀት ዓመቱ የሚዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለቀጣይ ዓመት መስኖና የመኽር እርሻ ጥቅም ላይ ለማዋል ከወዲሁ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። በማዳበሪያ ዝግጅቱ እየተሳተፉ ካሉት መካከል በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ታደሰ አለሙ በሰጡት አስተያየት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀትና መጠቀም ከጀመሩ ከ15 ዓመት በላይ እንደሆናቸው ገልጸዋል። በተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘገጃጀት ላይ ከግብርና ባለሙያዎች ባገኙት የካበተ ልምድና ዕውቀት በዓመት እስከ 23 ሜትር ኩብ ኮምፖስት ማዳበሪያ በጥራት አዘጋጅተው እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል። የሚያዘጋጁትን ኮምፖስት ማሳቸው ላይ በመጨመር የአፈር ለምነትን ከማሻሻል ባለፈ የሰብል ምርታማነትና ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን አመልክተዋል። የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅተው መጠቀም ከጀመሩ ወዲህ ለምነቱን አጥቶ ከምርት ውጭ ሆኖ የቆየ ግማሽ ሄክታር መሬት ለምነቱ መመለሱን የገለጹት ደግሞ በዞኑ የሰከላ ወረዳ አርሶ አደር ፈጠነ አስረስ ናቸው። ከዚህም በየዓመቱ እስከ 12 ኩንታል የስንዴና የገብስ ምርት በመሰብሰብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው፣ በተያዘው በጀት ዓመትም 18 ሜትር ኩብ ኮምፖስት በጥራት አዘጋጅተው ለመጠቀም ወደሥራ መግባታቸውን ተናግረዋል። የቢሮው መረጃ እንደሚያመለክተው በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተዘጋጀ ከ81 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለመስኖና ለመኸር ሰብል ልማት ጥቅም ላይ መዋሉ ታውቋል።  
በዞኖች ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ውጤታማ ናቸው
Aug 19, 2026 88
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወነ ያለው ተግባር ውጤታማ መሆኑን የጉራጌ፣ ስልጤና ከምባታ ዞኖች አስታወቁ። በስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ሁሴን እንዳሉት፣ በዞኑ የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማሳደግ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተደረገ ባለው ጥረት ውጤት ተመዝግቧል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በራስ አቅም ሰብዓዊ ድጋፍን ለመሸፈን የሚውል የእህል ክምችት ለመያዝ በተከናወነ ተግባር፣ እስከ አሁን ከ11 ሺሕ 860 ኩንታል በላይ ምርት በወል መሬት ላይ አምርቶ ማከማቸት እንደተቻለ ገልጸዋል። በተጨማሪም ማህበረሰቡን በማሳተፍ 22 ሚሊዮን ብር በጥሬ ገንዘብና የተለያዩ ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ ማከማቸት ተችሏል ብለዋል። በተያዘው የበጀት ዓመትም በዞኑ በመኸር ወቅት 207 ሄክታር ማሳ በበቆሎ ሰብል ለዚሁ ተግባር እየለማ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በተጨማሪም 30 ሚሊዮን ብር በማሰባሰብ ለሚከሰቱ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   በጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጊዜወርቅ አለሙ በበኩላቸው፣ ለተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በማህበረሰብ ተሳትፎ 6 ሺሕ 800 ኩንታል እህል ማከማቸት ተችሏል ብለዋል። በተያዘው የበጀት ዓመትም በዞኑ በመኸር ወቅት 260 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች የለማ ሲሆን ፣ ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ የመጠባበቂያ ገንዘብ ለማሰባሰብ ግብ ተጥሎ ወደ ትግበራ መገባቱን አመልክተዋል።   በከምባታ ዞን ግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አስራት ማቲዎስ እንደገለጹት ደግሞ፣ በዞኑ በተለያዩ ምክንያቶች ለሚከሰቱ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዲቻል ከማህበረሰቡ ጋር ስምምነት ላይ ተደርሷል። በዚህም 480 ኩንታል የምግብ እህል ከማምረት ባሻገር፣ 22 ሚሊዮን ብር በጥሬ ገንዘብ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል። በመኸር እርሻም 180 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች እየለማ ሲሆን 124 ሚሊዮን ብር ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል።    
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ ነው
Aug 19, 2026 116
ወላይታ ሶዶ ፤ ነሐሴ 13/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አስቴር ዳዊት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ ትግበራ በስኬትና በውጤታማነት ተጠናክሮ መቀጠሉ ይታወቃል።   የዲጂታል መሠረተ ልማቶች መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሳይበር ጥቃቶችን የመከላከልና የሳይበር ሉዓላዊነትን የማስከበር ተግባርም በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል። ይህንኑ ተግባራዊ ጥረት ለማጠናከርም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ከተለያዩ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የወጣቶችን የሳይበር ደህንነት ክህሎት የሚያሳድጉ የክረምት ስልጠና ፕሮግራሞችን በማካሄድ ላይ ይገኛል።   በተለይም የክረምት የስልጠና መርሃ-ግብር በሳይበር ደህንነት፣ በሶፍትዌር ልማት፣ በኮዲንግ እና በመረጃ ደህንነት ዙሪያ የተሻለ ክህሎት ያላቸውን ታዳጊና ወጣቶች በመሰልጠን ላይ ናቸው። በዚሁ መሰረትም የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በክረምቱ በአምስተኛ ዙር በርካታ ወጣቶችን የሳይበር ደህንነት ስልጠና በመስጠት ላይ ሲሆን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አስቴር ዳዊትና ሌሎች የመንግስት ስራ ኃላፊዎች በስፍራው በመገኘት ሰልጣኞችን አበረታትተዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የወጣቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን አንስተው በዚሁ መሰረትም የስልጠና እና ግንዛቤ ስራዎች መቀጠላቸውን ገልጸዋል። በክረምቱ ወላይታ ሶዶን ጨምሮ በስድስት ዩኒቨርሲቲዎች ለወጣቶች ተመሳሳይ ስልጠና በመሰጠት ላይ መሆኑን አንስተው ይህም ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም የሚሆን ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን አንስተው ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል።   የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳይ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት አክበር ጩፎ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ብቁ ዜጎችን የማፍራት ስራውን መቀጠሉን ገልጸዋል። ከቴክኖሎጂ፣ ከኢንዳስትሪና መሰል ተቋማት ጋር የመስራት ዕድል መፈጠሩን ጠቁመው ይህም የተለየ ተሰጥኦ ላላቸው ተማሪዎች መልካም እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።   ከሰልጣኞቹ መካከል ከዲላ ከተማ የመጣችው የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው መልካም አስራት እና ከሐዋሳ ከተማ የመጣችው የ11ኛ ክፍል ተማሪ ኖሐሚን ንጋቱ፤ በስልጠናው ስለ የሳይበር ደህንነትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ መሰረታዊ ዕውቀት በመገብየት በዲጂታሉ ዓለም የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረን አድርጎናል ብለዋል። የወላይታ ሶዶ ነዋሪና በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ ዓመት ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ፍሬው ቶማስ በበኩሉ ይህ ስልጠና ክህሎታቸውን ለማሳደግ አማራጭ ላጡ ወጣቶችና ተማሪዎች መልካም ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል።   በስልጠናው የሳይበር ደህንነት እውቀት ማግኘቱን የጠቀሰው ወጣቱ የመረጃ መንታፊዎችን በመዋጋት የሀገራችንን የመረጃ ደህንነት ለማረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ አረጋግጧል ።
መሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻል ዜጎች ያለ እንግልት የሚገለገሉበት ነው
Aug 19, 2026 148
አሶሳ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፡- መሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻል ዜጎች ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ ገለጹ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አራተኛው የበለስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ ጀምሯል።   ማዕከሉ ስራ በጀመረበት ወቅት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ እና የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አስካለች አልቦሮ ተገኝተዋል። ‎የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ በወቅቱ እንደተናገሩት፣በበለስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ8 ተቋማት እና 36 አገልግሎቶች ስራ ጀምሯል። ‎በለስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ ወደሥራ የገባ አራተኛው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሲሆን በቀጣይም አገልግሎቱን በመጨመር የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።‎ በክልሉ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ በ124 የአገልግሎት ዘርፎች ከ53 ሺ 900 በላይ ዜጎች የአገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። ‎‎የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎቱ ቁልፍ የሆኑ የክልልና የፌደራል ተቋማትን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ እያስቻለ መሆኑን ጠቅሰዋል።   ‎የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አስካለች አልቦሮ በበኩላቸው፤ የመንግሥት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸውን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ በሥርዓት ወደ ሚመራ ተቋማዊ ብቃት እየተሸጋገሩ መሆኑን መሶብ የአንድ ማዕከል አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። ‎‎የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውጤታማ መሆን የሚችሉት በመንግስት ተቋማት በሚሰጠው አገልግሎት የዜጎች እርካታን ማሳደግ ሲቻል እንደሆነ ጠቅሰዋል። በክልሉ ቀደም ‎የቤጉ ፣ የአሶሳ እና የባምባሲ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን ይታወሳል
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አራተኛ የሆነው የበለስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመረቀ
Aug 19, 2026 88
‎አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ) ፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አራተኛ የሆነውን የበለስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ እና የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አስካለች አልቦሮ መርቀው ከፍተዋል። አቶ ጌታሁን አብዲሳ ማዕከሉን በመረቁበት ወቅት እንደተናገሩት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻል የዜጎችን እንግልት የሚያስቀር ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው።   ‎የበለስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ አራተኛው ማዕከል መሆኑን ገልጸው ፣ የቤጉ መሶብ፣ የአሶሳ እና የባምባሲ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ቀደም ሲል ወደ ሥራ መግባታቸውን አስታውሰዋል።   ‎በክልሉ በተዘረጋው ዘመናዊ የአገልግሎት ስርዓት እስካሁን በ124 የአገልግሎት ዘርፎች ከ53 ሺ 900 በላይ ዜጎች የዲጂታል አገልግሎት ያገኙ ሲሆን፣ የእርካታ ደረጃውን 99.2 ከመቶ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል። በሁሉም የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ቁልፍ የክልሉና የፌዴራል የመንግሥት ተቋማት በአንድ ማዕከል መስጠት መቻሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። ‎አሰራሩ መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ከብልሹ አሰራር የፀዱ ከማድረጉም ባሻገር በጥራትና በፍጥነት አገልግሎቱን ለመስጠት ማስቻሉን ገልጸው ይህም ዜጎች በመንግሥት ላይ ያላቸውን አመኔታ እንደሚያሳድግም ጠቁመዋል። ህዝቡ እየታየ ያለውን ሰላም ወደ ዘላቂነት ለማሻገር ከፀጥታ አካላት ጋር ተባባሪ ሊሆን እንደሚገባም አቶ ጌታሁን አሳስበዋል።   ‎የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አስካለች አልቦሮ በበኩላቸው፣ የመንግሥት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸውን በቴክኖሎጂ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት ለመሸጋገር መሶብ አንዱ ማሳያ መሆኑን ገለጸዋል። ‎የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውጤታማ መሆን የሚችሉት በመንግስት ተቋማት በሚሰጠው አገልግሎት የዜጎችን እርካታ ማሳደግ ሲቻል እንደሆነም ጠቅሰዋል። ‎የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አሳዬ አበበ፣ የማዕከሉ ሥራ መጀመር በዜጎች አገልግሎት አሰጣጥ ላይ በህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን እንደሚቀርፍ ተናግረዋል። ‎አመራሮቹ በበለስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
ከሰመራ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት አግኝተናል-ተገልጋዮች
Aug 19, 2026 422
ሰመራ፣ ነሀሴ 13/2018 (ኢዜአ)፡-የሰመራ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አሰራር በመዘርጋቱ ጊዜና ገንዘባቸውን ለመቆጠብ መቻላቸውን ተገልጋዮች ገለጹ። ማዕከሉ ጉዳይ ለማስፈጸም የተለያዮ ቢሮዎች ለመሄድ ይገደዱ የነበረበትን አሰራር ማስቀረቱን የተናገሩት ተገልጋዮቹ፣ በአሁኑ ወቅት በአንድ ቦታ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የማዕከሉ ተገልጋዮች መካከል አቶ ኢብራሂም አሚን የንግድ ፈቃድ ለማደስና ግብራቸውን ለመክፈል ወደማዕከሉ እንደመጡ ገልጸዋል። በማዕከሉም ሁሉንም አገልግሎት ፈጣን በሆነ መንገድ እንዳገኙ ገልጸው ይህም ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ጉዳይ ለማስፈጸም ወደተለያዩ ቢሮዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን ወጪና እንግልት አስቀርቷል ብለዋል። ቀደም ሲል ጉዳይ ለመፈጸም በርካታ ቀናት ሲወስድባቸው እንደነበር አስታውሰው በአሁኑ ወቅት በጥቂት ደቂቃ ውስጥ ጉዳያቸውን እንደጨረሱ ተናግረዋል። በማዕከሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር በመዘርጋቱ በርካታ አገልግሎቶች በአንድ ቦታ ማግኘት እንደቻሉና በዚህም ደስተኛ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተገልጋይ አቶ ዓሊ ኢብራሂም ናቸው። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩትን ብልሹ አስራሮችን ሙሉ በሙሉ ማስቀረቱን ጠቁመው፣ በማዕከሉ በጥቂት ደቂቃ ውስጥ የንግድ ፍቃድ ለማውጣት የሚያስችል የመለያ ቁጥር ማግኘታቸውን ተናግረዋል። በማዕከሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ማውጣት እንደቻሉ የገለጹት ደግሞ መርዲያ ኑርሁሴን እና ፋጡማ ሀቢብ ናቸው። በዚህን ያህል ፍጥነት አገልግሎቱን እናገኛለን ብለው ያስቡ እንዳልነበር ገልጸው፣ በማዕከሉ ፈጣን አገልግሎት ከጥሩ መስተንግዶ ጋር በማግኘታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።   የሰመራ ከተማ ሞሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ ረዳት ፕሮፌሰር ከሊል ዓሊ በበኩላቸው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልል ደረጃ መሰጠት መጀመሩን ገልጸዋል። ይህም በተለያየ ቦታ ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን ባንድ ቦታ በዲጂታል አሰራር ታግዞ ለመስጠት አስችሏል ብለዋል። ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ከማስቻሉ በተጨማሪ የተገልጋይን ጊዜና ገንዘብ ከብክነት እየታደገ መሆኑንም ተናግረዋል። አገልግሎቱ ዘመኑን የዋጀ መሆኑን ጠቅሰው፣ በክልል ደረጃ መሰጠት የጀመረውን አገልግሎት በሰመራ ሎጊያ፣ በአዋሸ ሰባት እና በአይሳኢታ ከተሞች ለማስፋፋት የማዕከላት ግንባታ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም አብአላ፣ ዱብቲ፣ ሚሌ፣ ጭፍራ እና ወረር አዳብቶሌ ከተሞች የቦታ መረጣና ልየታ ሥራ ተከናውኗል ብለዋል። እንደ ዋና ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ግንባታቸውን በመከናወን ላይ ያሉት ማዕከላት በበጀት ዓመቱ ሩብ ዓምት ድረስ አገልግሎት ለማስጀመር ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። የሰመራ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአምስት ተቋማት ዘጠኝ አገልግሎቶች ስራውን መጀመሩን አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት የሚሰጡ አገልግሎቶች ወደ 41 ከፍ ማለታቸውንና በቀጣይም ወደ 80 ለማድረስ መታቀዱን ተናግረዋል። በማዕከሉ አገልግሎት ከሚሰጡት ውስጥ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ ፍትህ ቢሮ እንዱሁም ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) እንደሚገኙበት ገልጸው፣ እስካሁንም በማዕከሉ 20 ሺሀ 463 ተጠቃሚዎች አገልግሎት አግኝተዋል ብለዋል።
ስፖርት
ካሜሮን ለመጀመሪያ ጊዜ የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫን አነሳች
Aug 17, 2026 272
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በ14ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ካሜሮን ማላዊን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በሞሮኮ ራባት በሚገኘው የሙላይ አል ሀሰን ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ካሜሮን ፍጹም የበላይነትን ወስዳለች። ማሪ ንጋህ በ20ኛው እና በ45ኛው ደቂቃ ላይ ሁለት ግቦችን ከመረብ ስታሳርፍ፣ ናኦሚ ንጆአ ኤቶ በ30ኛው ደቂቃ ላይ ሶስተኛዋን ግብ አክላለች። ማላዊ በሁለተኛው አጋማሽ ጥሩ እንቅስቃሴ ብታደርግም የካሜሩንን የተከላካይ ክፍል ሰብራ ግብ ማስቆጠር አልቻለችም። ካሜሮን ውጤቱን ተከትሎ የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫን ለመጀመሪያ ጊዜ አንስታለች። የማይበገሩት አንበሶች ከዚህ ቀደም ሶስት ጊዜ ለፍጻሜ ደርሰው ማሸነፍ አልቻሉም ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ ለፍጻሜ የቀረበችው ማላዊ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ይህ ድል ለካሜሩን የዋንጫ ክብር ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማትንም ያስገኘ ነው። አሸናፊዋ ካሜሩን ከአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሁለት ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ ሽልማት የምታገኝ ሲሆን፣ ይህ ስኬት ቡድኑን በቀጥታ እ.አ.አ በ2027 በብራዚል ለሚካሄደው 10ኛው የፊፋ የሴቶች የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን ያረጋገጠላት ሆኗል። ከካሜሩን በተጨማሪ ግማሽ ፍጻሜ የደረሱት ማላዊ፣ ሞሮኮ እና ናይጄሪያም አፍሪካን ወክለው በዚህ ታሪካዊ የዓለም ዋንጫ ላይ ይሳተፋሉ። ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው ማላዊ የ750 ሺህ ዶላር ሽልማት ይበረከትላታል። አዘጋጇን ሞሮኮን በደረጃ ጨዋታ በመለያ ምት በመርታት ሶስተኛ የወጣችው አልጄሪያ የ550 ሺህ ዶላር ሽልማት ታገኛለች። ሞሮኮ የ300 ሺህ ዶላር ሽልማት ወደ ካዝናዋ ታስገባለች። ሞኒክ ንጎክ (ካሜሩን) የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች በመባል ተመር ጣለች። ሚካኤሊ ቢሂና (ካሜሩን) በውድድሩ ላይ ባሳየችው ብቃት ኮከብ ግብ ጠባቂ ሆናለች። ቴምዋ ቻዊንጋ (ማላዊ) አምስት ግቦችን በማስቆጠር የኮከብ ግብ አግቢነቱን የወርቅ ጫማ ወስዳለች። ከሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሞሮኮ በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ 12 ሀገራት ተሳትፈውበታል።
በሀዋሳ ከተማ በኮሪደር ልማት የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታን ፈጥረዋል--ከንቲባ ጥራቱ በየነ
Aug 16, 2026 353
ሀዋሳ፤ ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- በሀዋሳ ከተማ በኮሪደር ልማት የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎቸ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታን መፍጠራቸውን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ። “ኮሪደር ልማት ለስፖርት ቱሪዝም” በሚል መሪ ሀሳብ የታዳጊዎችና ወጣቶች የፕሮጀክት ስፖርታዊ ውድድር በሀዋሳ ከተማ ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ እንዳሉት፣ ወጣቶችና ሕጻናት በስፖርቱ ዘርፍ በንቃት እንዲሳተፉ በማድረግ የነገ ተተኪ ስፖርተኞች እንዲሆኑ ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።   በከተማዋ የሚካሄዱ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ወጣቶችን፣ ሕጻናትንና አረጋውያንን ታሳቢ ያደረጉ ምቹ የመዝናኛ፣ የማረፊያና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ያካተቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በስፖርቱ ዘርፍ ሀዋሳ ከተማን፣ የሲዳማ ክልልንና ሀገርን የሚወክሉ ስፖርተኞችን ለማፍራት በአራት ዙር በተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች 15 የሕጻናት መጫወቻ፣ የወጣቶችና ታዳጊዎች ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታዎች በዕቅድ መካተታቸውን አብራርተዋል። ከነዚህም ሦስት የታዳጊዎችና ሦስት የወጣቶች (በጠቅላላው ስድስት) ሰው ሰራሽ ሣር የተነጠፈላቸው የእግር ኳስ ሜዳዎች፣ 4 የቅርጫት ኳስ ሜዳዎች፣ 5 የሕጻናት መጫወቻ ስፍራዎችና የሜዳ ቴኒስ ማዘውተሪያዎች መገንባታቸውን ገልጸዋል። እነዚህም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታን መፍጠራቸውን አመልክተዋል።   አቶ ጥራቱ አክለውም፤ ወጣቶች የእረፍት ጊዜያቸውን በአልባሌ ስፍራ ከማሳለፍ በመራቅ በስፖርት ላይ እንዲያተኩሩና እነዚህን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በአግባቡና በጥንቃቄ እንዲይዟቸው አሳስበዋል። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ በላይነሽ ገዳ በበኩላቸው፣ በከተማዋ በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ለአምስት ቀናት የሚቆይና በእግር ኳስ፣ በቅርጫት ኳስ፣ በብስክሌትና በሜዳ ቴኒስ በሁለቱም ጾታዎች 34 ቡድኖች የሚሳተፉበት የፕሮጀክቶች ስፖርታዊ ውድድር መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የተገነቡት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ለክልሉ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራትና ለዘርፉ መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ የገለፁት ደግሞ የሲዳማ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዶማርሶ ዶና ናቸው። በፕሮጀክት ውድድሩ ላይ ተሳታፊ ከሆኑ ስፖርተኞች መካከል ወጣት ፍላጎት ተሻ እና ወጣት ሚካኤል ፍጹም እንደገለጹት፣ በከተማዋ የተገነቡት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ባላቸው ፍላጎትና ተሰጥኦ መሠረት እንዲሳተፉ አስችሏቸዋል። በክረምቱ ወቅት በተለያዩ መስኮች በፕሮጀክት ታቅፈው ሲሰለጥኑ መቆየታቸው ጊዜያቸውን አልባሌ ቦታ ላይ እንዳያባክኑ ትልቅ እድል እንደፈጠረላቸውም አክለዋል። በስነ-ሥርዓቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩና የክልሉ አመራሮች እንዲሁም ወጣቶች ተገኝተዋል።  
አርሰናል ማንችስተር ሲቲን 3 ለ 0 በማሸነፍ የኮሙኒቲ ሺልድ ዋንጫን ለ18ኛ ጊዜ አነሳ
Aug 16, 2026 350
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ):- አርሰናል ማንችስተር ሲቲን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት በማሸነፍ የ2026 የኤፍኤ ኮሙኒቲ ሺልድ ዋንጫን ለ18ኛ ጊዜ አሳክቷል። በዌልስ መዲና ካርዲፍ በሚገኘው ታሪካዊው ፕሪንሲፓሊቲ ስታዲየም በተካሄደው የውድድር ዘመን መክፈቻ ጨዋታ፤አርሰናል በጨዋታው ላይ ፍጹም የበላይነት በመውሰድ ነው ማንችስተር ሲቲን ማሸነፍ የቻለው። ለአርሰናል የማሸነፊያ ግቦቹን ተከላካዩ ሪካርዶ ካላፊዮሪ፣ አጥቂው ካይ ሃቨርትዝ እና የቡድኑ አንበል ማርቲን ኦዲጋርድ አስቆጥረዋል። ከ22 ዓመታት በኋላ የፕሪሚየር ሊጉን ክብር የተቀዳጀው አርሰናል እና በኤፍኤ ካፕ ፍፃሜ ቼልሲን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለዚህ ጨዋታ የበቃው ማንቸስተር ሲቲ ያደረጉት ይህ ጨዋታ፤ አርሰናል በኮሙኒቲ ሺልድ መድረክ በማንቸስተር ሲቲ ላይ ያለውን ፍጹም የበላይነት አስቀጥሏል። ሁለቱ ቡድኖች በዚሁ መድረክ ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው ሶስት ጨዋታዎች በሙሉ አርሰናል ያሸነፈ ሲሆን፣ የዛሬው ድል በዚሁ መድረክ በማንቸስተር ሲቲ ላይ ያስመዘገበውን አራተኛ ተከታታይ ድል አድርጎታል። አርሰናል የዋንጫ ቁጥሩን ወደ 18 በማሳደግ በውድድሩ ታሪክ 21 ዋንጫዎችን በማንሳት የመጀመሪያውን ደረጃ ከያዘው ማንቸስተር ዩናይትድ ቀጥሎ ያለውን ስኬታማነት አጠናክሯል።
አርሰናል ከማንችስተር ሲቲ የኮሙኒቲ ሺልድ ዋንጫን ለማንሳት የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Aug 16, 2026 355
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 10 /2018 (ኢዜአ):- የ2026 የኮሙኒቲ ሺልድ የዋንጫ ጨዋታ በአርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ መካከል ዛሬ ይካሄዳል። ጨዋታው ከቀኑ 11 ሰዓት በዌልስ መዲና ካርዲፍ በሚገኘው ታሪካዊው ፕሪንሲፓሊቲ ስታዲየም ይካሄዳል። ይህ ተጠባቂ የውድድር ዘመን መክፈቻ ጨዋታ የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነውን አርሰናልን እና የ2026 የኤፍኤ ካፕ አሸናፊውን ማንቸስተር ሲቲን ያገናኛል። አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ የፕሪሚየር ሊጉን ክብር በመቀዳጀት፣ ማንቸስተር ሲቲ ደግሞ በኤፍኤ ካፕ ፍፃሜ ቼልሲን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለዛሬ ጨዋታ ቀርበዋል። በኮሙኒቲ ሺልድ ታሪክ አርሰናል በማንቸስተር ሲቲ ላይ ፍጹም የበላይነት እንዳለው መረጃዎች ያሳያሉ። ሁለቱ ቡድኖች በዚሁ መድረክ ከዚህ ቀደም ሶስት ጊዜ የተገናኙ ሲሆን በሶስቱም ጨዋታዎች አርሰናል አሸንፏል። ቡድኖቹ ለመጨረሻ ጊዜ እ.ኤ.አ በ2023 ባደረጉት የኮሙኒቲ ሺልድ ጨዋታ አርሰናል በመለያ ምት ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ጨዋታው ከዚህ ቀደም በለንደኑ ዌምብሌይ ስታዲየም ይደረግ የነበረ ሲሆን በዚህ ዓመት ዌልስ መዲና ካርዲፍ በሚገኘው ታሪካዊው ፕሪንሲፓሊቲ ስታዲየም እንዲዘዋወር ተደርጓል። ይህም የሆነበት ምክንያት በዌምብሌይ ስታዲየም ቀድሞ የተያዘ የሙዚቃ ኮንሰርት በመኖሩ እንደሆነ ታውቋል። ይህም ውድድሩ ከ20 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዌልስ መዲና እንዲመለስ አድርጎታል። የ34 ዓመቱ ሳም ባሮት ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የኮሙኒቲ ሺልድ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረው እ.ኤ.አ በ1908 "የኤፍኤ ቻሪቲ ሺልድ" በሚል ስያሜ የነበረ ሲሆን በኋላም እ.ኤ.አ በ2002 አሁን ወደሚጠራበት "ኤፍኤ ኮምዩኒቲ ሺልድ" ስያሜ ተቀይሯል። ውድድሩ የሊጉን ሻምፒዮን እና የኤፍኤ ካፕ አሸናፊውን በማገናኘት አዲሱ የውድድር ዘመን በይፋ መጀመሩ የሚበሰርበት ነው። ከጨዋታው ትኬት ሽያጭ እና ማስታወቂያ የሚሰበሰበው ገቢ በሙሉ በእንግሊዝ ዙሪያ ለሚገኙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና የማህበረሰብ እግር ኳስ ልማት ስራዎች ይውላል። ማንቸስተር ዩናይትድ 21 ጊዜ በማሸነፍ የውድድሩ ስኬታማ ክለብ ነው። አርሰናል 17 ዋንጫዎችን በማንሳት ይከተላል። ማንቸስተር ሲቲ ደግሞ ሰባት ጊዜ አሸንፏል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት ኖርዌይ ትደግፋለች
Aug 19, 2026 163
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ ኖርዌይ ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትደግፍ በኢትዮጵያ የኖርዌይ ኤምባሲ የደንና አየር ንብረት ጉዳዮች ልዩ መልዕክተኛና አማካሪ ላይቭ ጃኮብ ሲድነስ ገለጹ። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ስጋት የሆነውን የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ለመከላከል በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ በአረንጓዴ ልማትና በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ለቀጣናው ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ተግባር በማከናወን ላይ ትገኛለች። በኢትዮጵያ የኖርዌይ ኤምባሲ የደንና አየር ንብረት ጉዳዮች ልዩ መልዕክተኛና አማካሪ ላይቭ ጃኮብ ሲድነስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በደን ልማት ዘርፍ አስደናቂ ለውጥ ተገኝቷል፡፡   በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርና በአፈርና ውሃ ጥበቃ በተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በሀገሪቱ የደን ሽፋን ላይ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ ኖርዌይ ባለፉት አስርት ዓመታት ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የደን ሽፋን ማሳደግ የሚያስችል እንቅስቃሴ አድርገናል ብለዋል፡፡ የደን ልማት የአፈር መሸርሸርን መከላከልና የአፈርና ውሃ ሀብት ጥበቃ በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንደሚያሳድግ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የደን ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ በቀጣናው የውኃ አቅርቦትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እገዛ እንደሚያደርግም ተናግረዋል፡፡ ኖርዌይ ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትደግፍም ገልጸዋል። ሁለቱ ሀገራት በደን ጥበቃ ስራዎች በመተባበር የደን ጭፍጨፋን ለመቀነስ እንደሚሰሩ ጠቅሰው፤ ኖርዌይ የኢትዮጵያ የሬድ ፕላስ መርሃ ግብር ትግበራ ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኗን ተናግረዋል።   በኢትዮጵያ የተነደፈውን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የሚቋቋም አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ለመደገፍ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥልም ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ዘመናዊ የከተሜነት የሥነ-ምኅዳር ከባቢ አጎናፅፏታል
Aug 18, 2026 259
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ውጤታማነት ዘመናዊ የከተሜነት የሥነ-ምኅዳር ከባቢ እንዳጎናጸፋት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ገለጸ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ እየተካሄዱ ያሉትን የኮሪደር፣ የወንዞችና የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን አስመልክቶ ከአካባቢ ጥናት አማካሪ ድርጅቶች ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ እሸቱ ለማ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ የልማት ፕሮጀክቶች ከአካባቢና ከማህበረሰብ ደህንነት ጋር ተጣጥመው እንዲሄዱ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ (EIA) እና ኦዲት ጥናቶች ወሳኝ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተቋማቸው ደረጃውን የጠበቀና ተወዳዳሪ ለመሆን የሪፎርም ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ከአማካሪ ድርጅቶች የሚገኙ ግብዓቶች ተቋማዊ አሰራሩን ለማዘመንና የታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት እንደሚረዱም ነው የገለጹት። በባለሥልጣኑ የአካባቢና ማህበረሰብ ተፅዕኖ ግምገማ ቡድን መሪ አቶ አብዲ ቀሊ በበኩላቸው፤ አማካሪ ድርጅቶች የሚያቀርቧቸው የጥናት ሰነዶች በጥራትና በሳይንሳዊ ደረጃቸው ብቁ ሊሆኑ እንደሚገባ አስረድተዋል። የመድረኩ ዋና ዓላማ የብክለት መጠንን በጥናት በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫ ማስቀመጥ መሆኑም ተጠቁሟል።
በፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር ቅንጅታዊ ሥራዎች ቀጥለዋል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Aug 17, 2026 159
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ) ፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማና አምራች ዜጋን በመፍጠር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ ሥራዎች መቀጠላቸውን የክልሉ ርዕሰመስተዳደር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ። "ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" በሚል መሪ ሀሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ ለ3ኛ ዙር የተዘጋጀ የፅዱ ኢትዮጵያ የንቅናቄና የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል። ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ እንዳሉት በክልሉ በፅዱ ኢትዮጵያ ጤናማና አምራች ዜጋን በመፍጠር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ ሥራዎች ቀጥለዋል። ንቅናቄው ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር እያገዘ እንደሚገኝ ገልጸው፣ በቀጣይም ህዝቡን ባለቤት በማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ይሰራል ብለዋል። ለዚህም ጽዳትን ባህሉ ያደረጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አመልክተዋል። የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ የአመራሩንና የባለድርሻ አካላትን ርብርብ ወሳኝ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በበኩላቸው እንዳሉት በመደመር መንግስት እሳቤ የአካባቢ ጥበቃ ሥራን በጋራ በማከናወን ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል።   የጽዱ ኢትዮጵያ ቀጣይ 3 ወራት ንቅናቄም ፕላስቲክን በአግባቡ የመጠቀም፣ የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው የፋብሪካ ኬሚካሎች አወጋገድና የድምጽ ብክለትን መከላከል ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል። የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ለተተኪው ትውልድ ጤናማና ምቹ አካባቢን ለማስተላለፍ የሚከናወኑ ተግባራት እንደሚጠናከሩም አክለዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ አብርሃም መጫ እንደገለጹት በክልሉ የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ትግበራ የተራቆተ መሬትን በማልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አስችሏል።   ከዚህ በተጨማሪ የከተሞችን ውበት ማስጠበቅን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ውጤቶች እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል። ቢሮው በቀጣይ 3 ወራት በሚተገበረው የፅዱ ኢትዮጵያ ኢንሼቲቭ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።   በመድረኩ የክልሉ፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እና ተጋባዥ እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
በጉጂ ዞን በዘንድሮው ክረምት በ16 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ምርጥ የቡና ችግኝ ተተክሏል
Aug 15, 2026 251
አዶላ፤ ነሐሴ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በዘንድሮው ክረምት በ16 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸው የቡና ችግኞች መተከላቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። የጉጂ ዞን በምርጥ መዓዛው እና ጣዕሙ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ዋጋ ከሚሸጡ ልዩ የቡና ዓይነቶች መካከል አንዱ የሚገኝበት አካባቢ ነው። የምድር ለምነት፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የደጋ አየር ጸባይ ዞኑ በቡና ልማት ተራጭቶ እንዲታወቅ አድርጎታል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዞኑ የሚገኙ አርሶ አደሮች የምርት ጥራት እና መጠንን ለማሳደግ ከተለምዷዊ አሰራር ወጥተው ሳይንሳዊ ዘዴዎችን እንዲከተሉ ሲደረግ ቆይቷል። በዘንድሮው ክረምት በዞኑ ምርትንና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ አርሶ አደሩን ከዘልማድ አሠራር አውጥቶ በተሻሻሉ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡና በሽታን በሚቋቋሙ አዳዲስ የቡና ዝርያዎች ተጠቃሚ ለማድረግ ሰፊ የችግኝ ተከላና የልማት እንቅስቃሴዎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ።   በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የቡናና ሻይ ልማት ባለሙያ አቶ ብርሃኑ ፈይሳ በዞኑ በዘንድሮ ክረምት የቡና ልማቱን በማስፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ ነው። የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸውና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ከ72 ሚሊዮን 500 ሺህ በላይ የቡና ችግኞች እስካሁን በ16 ሺህ 233 ሄክታር መሬት ላይ መተከላቸውን ገልጸዋል። አዲሱ ዝርያ ድርቅና በሽታን በመቋቋም ከአንድ ሄክታር እስከ 18 ኩንታል ምርት ለመስጠት የሚያስችል አቅም ያለው እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ ይህም ከነባሩ ዝርያ የሚገኘውን ከ7 ኩንታል በታች ምርት ከሁለት እጥፍ በላይ በማሳደግ አምራቹን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዞኑ በ12 ወረዳዎች እስካሁን የተተከለው የቡና ችግኝ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ13 ሚሊዮን ገደማ ብልጫ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። በልማቱም በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች ከ54 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን አስታውቀዋል፡፡ የዞኑ ንግድ ጽሕፈት ቤት ቤቱ ሃላፊ አቶ አሬሩ ዋሬ ከዞኑ በተሻሻለ ዝርያ እየተስፋፋ የመጣው የቡና ልማት፣ ምርቱን በብዛትም ሆነ በጥራት እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። ዘንድሮ ከዞኑ ከ231 ሺህ ኩንታል በላይ ቡና ለገበያ መቅረቡን ለአብነት አንስተዋል።   ምርቱ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ገበያ ተፈላጊነቱ እየጨመረ መምጣቱ ልማቱን ይበልጥ ለማስፋት ትልቅ የሥራ መነሣሣት መፍጠሩንም ኃላፊው ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሀገር አቀፍ የምርምር ማዕከላት ከፍተኛ ምርት የሚሰጡና የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ እንዲያቀርቡ መደረጉን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በዞኑ የሚገኙ በርካታ የእሼትና የደረቅ ቡና ኢንዱስትሪዎች ምርቱን በብዛትና በጥራት እያዘጋጁ ለገበያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ኃላፊው፤ የዞኑን የቡና ልማት ይበልጥ ለማስፋት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 873
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 806
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 1087
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1623
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
ቡሄ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ምስረታ ታሪካዊ ቁርኝት
Aug 19, 2026 97
በሙሴ መለሰ ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን የቡሄ በዓል በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ባለበት በዚህ ዕለት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አጀማመሩንና ምስረታውን ከዚህ በዓል ጋር ያለውን የጠበቀ ትስስር ወደ ኋላ መለስ ብሎ የሚታወስበት ነው። የክለቡ ምስረታና የቡሄ በዓል (የሆያ ሆዬ ጨዋታ) ቀጥተኛና የማይነጠል ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፣ ክለቡ በመስረታው ወቅት የነበረበትን የፋይናንስ እጥረት ቀርፎ የመጀመሪያውን ማሊያ ለመግዛት የበቃው በዚህ ዕለት በተሰበሰበ የሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ነበር። የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን መጀመሪያ ሲጠነሰስ በጆርጅ ዱካስና በአየለ አትናሽ አማካኝነት የነበረ ቢሆንም፣ ክለቡን በይፋ አደራጅቶ ለማቋቋም ግን የግድ የፋይናንስ አቅም ወይም ገንዘብ ያስፈልግ ነበር። ሆኖም ግን በሃገር ፍቅር ስሜት የተነሱት ዘጠኙ ወጣቶች ማለትም አየለ አትናሽ፣ ጆርጅ ዱካስ፣ ዮሐንስ ጥላሁን፣ ገብረመድህን ተፈሪ፣ ተፈራ ገብረእግዚአብሔር፣ ዓለማየሁ እጅጉ፣ መኮንን ደምሴ፣ አስፋው ያዕቆብ እና ክልቱ አያኖ ክለቡን በሚመሰርቱበት ወቅት ቤሳ ቤስቲን እንኳ ኪሳቸው ውስጥ ስላልነበራቸው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ተሰብስበው በሰፊው ተወያዩ። በዚህ የውይይት ወቅት ነው ገንዘብ ለማግኘትና የክለቡን መመስረት እውን ለማድረግ የቡሄ ቀን እጅግ መልካምና ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን የተረዱት። ዘጠኙ ወጣቶች በአንድ ድምፅ ተስማምተው በታሪካዊው የቡሄ ዕለት ማለትም ነሐሴ 13 ቀን 1927 ዓ.ም. በጋራ በመሆን ቡሄ ጨፍረው (ሆያ ሆዬ ብለው) በሚያገኙት ማናቸውም ነገር የክለቡን የመጀመሪያ ማሊያ ለመግዛት ቁርጥ የሆነ ውሳኔ ላይ ደረሱ። በዚያን ጊዜ የነበረው የባህል ልማድ አሁን ካለው የተለየ በመሆኑ፣ ቡሄ ሲጨፈር የሚሰጠው ጥሬ ገንዘብ ሳይሆን ሙልሙል ዳቦ ነበር። በመሆኑም ዘጠኙ ተጫዋቾችና መስራቾች ቀደም ሲል ከሚጨፍሩበትና ለምደውት ከነበረው አካባቢ ራቅ ብለው በመንቀሳቀስ በየቤቱ በር እያንኳኩ በደመቀ ሁኔታ ጨፈሩ፤ በዚህም ጥረታቸው በርካታ ቁጥር ያለው የሙልሙል ዳቦ በአንድነት ማሰባሰብ ቻሉ ታሪካዊውን ስራ ሰሩ። ይሁን እንጂ የተሰበሰበውን ይህንን በርካታ ዳቦ ወደ ጥሬ ገንዘብ ለመቀየር አዲስ አበባ ውስጥ ወደሚገኘው ሰራተኛ ሰፈር ለሚገኙ ወዛደሮች ለመሸጥ ዳቦውን በከረጢት ይዘው ጉዟቸውን ጀመሩ። በዚህ የጉዞ መስመር ላይ ሳሉ ግን ያልተጠበቀ ፈተና ገጠማቸው፤ በመንገድ ላይ ያገኟቸው “ዱርዬዎች” ከተሰበሰበው ዳቦ ላይ የተወሰነውን ነጠቋቸው። ወጣቶቹ ተስፋ ሳይቆርጡ ጉዟቸውን በመቀጠል የተረፈውን ዳቦ ለሰራተኛ ሰፈሩ ወዛደሮች በመሸጥ ማሊያ መግዣ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ በእጃቸው አስገቡ። ከዳቦው ሽያጭ የተገኘችው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን በወቅቱ መገበያያ በትክክል ሁለት ጠገራ ብር ነበረች። የክለባችው የመጀመሪያ መለያ ቡናና ነጭ ነበር። ቡናና ነጭ መሊያን የገዙት ግን ፈልገው አልነበረም በቂ ገንዘብ ስላልነበራቸው በሁለት ጠገራ ብር ከፒያሳ «ግሪካዊ አውግስታስ ዱስ» ከተባለ ሱቅ በርካሽ ስላገኙት ነበር። ይህ በቡሄ ዕለት የተጀመረው ታሪካዊ የማሊያ ግዢ በኋላ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በታህሣሥ ወር 1928 ዓ.ም. በይፋ ተመሠረተ። ክለቡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለብ በመሆን ታሪካዊ ማዕረግንና ቀዳሚነትን ተቀዳጀ። በ1928 ዓ.ም. በይፋ የተመሰረተው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በታሪኩ የመጀመሪያውን የሜዳ ጨዋታ ያደረገው ከ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ነበር። በዚሁ ታሪካዊ የመጀመሪያ ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። በዕለቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠንካራ ተፎካካሪ ከነበረው የ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ለመጫወት ወደ ሜዳ ሲያመራ፣ አስቀድመው ከተመረጡትና ቡድኑን ካደራጁት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ባልታወቀ ምክንያት ሳይመጣ ቀረ። በዚህ ድንገተኛ መቅረት ምክንያት ቡድኑ በሰው ጎደሎ ለመጫወት በተገደደበት ወሳኝ ሰዓት፣ መስራቾቹ በሜዳው አቅራቢያ መንገድ ላይ ሲጫወት ያገኙትን አንድ ታዳጊ ወጣት ተመለከቱ። ይህ ታዳጊ በወቅቱ ገና የ14 ዓመት ዕድሜ የነበረውና በኋላ ላይ የኢትዮጵያ ስፖርት ባልደረባ የሆነው ይድነቃቸው ተሰማ ነበር። ወጣቶቹም ያለ ምንም ቅድመ ዝግጅት ቡድኑን እንዲሞላ ድንገት ጋበዙት፤ እርሱም የቀረበለትን ጥሪ በደስታ ተቀብሎ በአጋጣሚ ወደ ሜዳ ገባ። ያለ ምንም ልምምድና ዝግጅት በድንገት የተሰለፈው ይድነቃቸው ተሰማ፣ በሜዳ ላይ ያሳየው አስደናቂ ችሎታና ቅልጥፍና ሁሉንም ያስገረመ ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ታሪካዊ ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ፣ ለክለቡ የመጀመሪያውን ድል ያስገኙትን ሁለቱንም ታሪካዊ የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ይኸው መንገድ ላይ ተገኝቶ በድንገት የተሰለፈው ታዳጊ ይድነቃቸው ነበር። ይህ ብቃት ገና በታዳጊነቱ በክለቡ ውስጥ ያለውን የማይተካ ቦታ ከማረጋገጡም በላይ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን የድል ጉዞ በደመቀ ሁኔታ እንዲጀመር አድርጓል። ቡሄ በዓል እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ያላቸው ታሪካዊ ቁርኝት የክለቡን ጥልቅ ህዝባዊና ባህላዊ መሰረት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቀዳሚ ፋና ወጊ የሆነው ይህ ታላቅ ክለብ፣ በታሪካዊቷ የነሐሴ 13 ቀን የቡሄ ዕለት የመስራቾቹ የ"ሆያ ሆዬ" ጨዋታና ከተሰበሰበው ሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ባገኟት ሁለት ጠገራ ብር የመጀመሪያውን ቡኒና ነጭ ማሊያ መግዛቱ፣ ክለቡ ከህዝብ ማህፀን የወጣ የህዝብ ሀብት መሆኑን ያረጋግጣል። ይህ ከባህልና ከትውፊት ጋር የተቆራኘ አስደናቂ አጀማመር፣ ከጊዜ በኋላ በ1928 ዓ.ም. ለይፋዊ ምስረታው በር ከፋች ከመሆኑም በላይ፣ በታሪካዊው የመጀመሪያ ጨዋታ ላይ እንደ ይድነቃቸው ተሰማ ያሉ የአፍሪካ እግር ኳስ ታላላቅ መሪዎችና ድንቅ ተሰጥኦዎች እንዲፈጠሩ መሰረት የጣለ የኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ነው።
ቡሄ የትውልድ ወጋገን፤ የማኅበራዊ ትስስር አምድ
Aug 19, 2026 103
ቡሄ በወርሃ ነሐሴ በ13ኛው ቀን ህፃናት ሆያ…. ሆዬ….! ሆ…. በሚል ዜማና ጅራፍ እያጮሁ የሚያከብሩት፤ እናቶች ለህፃናቱ ሙል ሙል ዳቦ በመስጠት እንኳን አደረሳችሁ እያሉ በድምቀት የሚያከብሩት በዓል ነው። ቡሄ ትርጓሜውም ብርሃን፣ብራ፣ ወጋግን ማለት ሲሆን ከጨለማ ወደ ብርሃን የመሸጋገሪያ የተስፋ ምልክት ነው። በሀይማኖታዊ አንድምታው በዓሉ የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ ብርሃን በደብረ ታቦር ተራራ ላይ መገለጡ የሚታሰብበት ነው፤ በዚህም ደብረ ታቦር ይባላል፡፡ የክረምቱ ጭጋግ ተገፎ የብርሃን ወጋገን የሚታይበት ሕፃናትና ወጣቶች በየቤቱ እየዞሩ «ሆያ ሆዬ» በማለት በረከትና ምርቃት የሚያፍሱበት የደስታና የፍቅር መግለጫ ነው። ህፃናትና ወጣቶች በየዕድሜያቸው ጅራፍ እያጮሁ በሕብረ ዝማሬዎች እየደመቁ በአብሮነት እና በደስታ የሚያከብሩት ትውፊታዊ በዓል ነው ቡሄ። የወጣቶችን ጉርብትና እና ማኅበራዊ ትስስር የሚያጎለብት እሴት ነው፤ በአከባበሩ ወቅት የሚንጸባረቀው የመረዳዳትና ያለውን የመካፈል ባህል ፋይዳውን ከትውልድ ወደ ትውልድ ማሸጋገር ያስችላል። የቡሄ በዓል ባህላዊ እሴቶችን በመጠበቅ፣ ትውልድን በማቀራረብ እና ማኅበራዊ ትስስርን ይበልጥ በሚያጠናክር ተምሳሌትነቱ እልፍ ነው። በአዲስ አበባ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከፍተኛ የቅርስ ጥናት ተመራማሪ መምህር መክብብ ገብረማሪያም ለኢዜአ እንዳሉት፤ የቡሄ በዓል የብርሃን ዘመን መምጣቱን የተስፋ ጎህ መቅደዱን ማብሰሪያ ነው፡፡ ቡሄ ከጨለማ ወደ ብርሃን ሽግግር መምጣቱን የሚያበስር በታዳጊዎች የሚዘከር የፍቅር፣ የአንድነትና የበረከት መገለጫና ተስፋ መሆኑን ያነሳሉ፡፡ ታዳጊዎችና ወጣቶች በበዓሉ ወቅት የሚያዜሙት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሸጋገር የመጣው የ«ሆያ ሆዬ» ሕብረ ዜማ ለጋራ ትርክት ግንባታ ገንቢ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል። ቡሄ የትውልድ ወጋገን፤ የማኅበራዊ ትስስር አምድ በመሆኑ ማኅበራዊ ትስስርና የጋራ ዕሴቶችን ማጠናከር ያስችላል ብለዋል።   ታዳጊው በሱፈቃድ አስሜ ቡሄ ከጓደኞቹ እና ከወዳጅ ዘመዶቹ ጋር ፍቅርንና አብሮነትን ይበልጥ የሚያጠናክርበት የደስታና የተስፋ በዓል መሆኑን ይናገራል፡፡ ቡሄ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠብቀውና ቀጣይ ሕይወቱን በአዲስ መንፈስ ለመምራት አቅም የሚፈጥርለት የብሩህ ዘመናትን ማለሚያ መሆኑን ይገልፃል። ቡሄ ከታላላቆቹ የወረሰው ከእኩዮቹ ጋር በፍቅርና በደስታ የሚያከብረው ነገን በተስፋ የሚያይበት ውብ በዓል እንደሆነ የሚናገረው ደግሞ ታዳጊው በረከት ምናለ ነው፡፡   የተጣሉ ጓደኛሞች እርቅ የሚያወርዱበት በዓል በመሆኑ ለትውልድ አንድነት እና አብሮነትን በማስተማር ረገድ ትልቅ ድርሻ አለውም ብሏል። ወጣት ያብስራ ጸጋዬ በበኩሉ ቡሄ በዓመት አንድ ጊዜ የሚመጣ፤ ተራርቀው ከሚኖሩ የተለያዩ አካባቢ እኩዮቹ ጋር በአንድነት የሚያከብሩት በዓል መሆኑን ይናገራል፡፡   ከሁሉም ዓይነት ሕብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ታዳጊዎች የሚሰባሰቡበት፤ ሕብረ ብሔራዊነትን የሚያጠናክር የጋራ በዓል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ በኃይሉ ሞገስ ናቸው።      
ሳምንቱን በወፍ በረር!!
Aug 16, 2026 196
ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ሳምንቱን በወፍ በረር!! በዚህ ዝግጅታችን በክልሎች የተከናወኑ ዓበይት ጉዳዮችን በወፍ በረር ቃኝተን እናስታውሳለን። በመሆኑም በሳምንቱ በተለያዩ የሀገራችን ክልሎች ከተከናወኑ ዓበይት ኩነቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ ምን ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 1. የሰሊጥ ልማት በጋምቤላ ከሳምንቱ ዓበይት ጉዳዮች መካከል በጋምቤላ ክልል በተያዘው የመኸር ወቅት ከ86 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥ ሰብል የመልማቱ ዜና አንዱ ነው። በክልሉ የቅባት እህሎች ልማት በዋናነት በባህላዊ አርሶ አደሮችና በጥቂት ባለሀብቶች ተወስኖ ሲከናወን የነበረ ቢሆንም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመናዊ የግብርና ግብዓቶች እና በሜካናይዜሽን እርሻ ታግዞ እየተካሄደ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታውቋል።   እንደ ቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ኡጀሉ ኡሞድ ገለጻ፤ ክልሉ የቅባት ሰብሎችን ጨምሮ ለሁሉም የግብርና ልማት ሥራዎች ምቹ ስነ-ምህዳር ያለው ነው። በክልሉ በዘንድሮው የመኸር ወቅት በባለሀብቶችና በአርሶ አደሮች ከ86 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥ ሰብል ለምቷል። ከዚህም ከ516 ሺህ ኩንታል በላይ የሰሊጥ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቁመው፣ በአሁኑ ወቅት የሰብሉ ቁመና በተሻለ ሁኔታ ላይ ስላለ ከተጠበቀው በላይ ምርት ሊገኝ እንደሚችልም ተንብየዋል። 2. የገቢ አሰባሰብን በማጠናከር ልማትን ማፋጠን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝብን የልማት ጥያቄ የመመለስ ተግባራት እንደሚጠናከሩ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የተገለጸውም በዚህ ሳምንት ነበር።   ርዕሰ መስተዳድሩ ይህን የተናገሩት የክልሉ ገቢዎች እና ንግድና ገበያ ልማት ቢሮዎች በሕገ-ወጥ የንግድ ቁጥጥር፣ ኑሮን ማረጋጋትና የታክስ ሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ በሆሳዕና ከተማ ባዘጋጁት የንቅናቄ መድረክ ላይ ነው። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች የመመለስ ተግባር እንደሚጠናከር ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ገቢን በማሳደግ የከተሞችን ገጽታ የመቀየር፣ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን የማስፋትና የማህበረሰቡን ሕይወት ለማሻሻል በተከናወኑ ተግባራት ስኬቶች እንደተመዘገቡና በቀጣይም ይህን ለማጠናከር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል በክልሉ የንግድ ሥርዓቱን በማዘመን የተሳለጠ አሠራር መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን የጠቆሙት እንዳሻው (ዶ/ር)፤ ለዚህም ሕገ-ወጥነትን የመከላከል፣ የግብይት ማዕከላትን የማስፋፋት፣ ምርትን በበቂ ሁኔታ የማቅረብ፣ የዋጋ ንረትን የመቆጣጠርና የሸማች ማኅበራትን የማጠናከር ሥራዎች እንደሚከወኑም አክለዋል። 3. የአፋር ክልል በጀት የክልሉ ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ33 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ያጸደቀውም በዚሁ ሳምንት ነበር። በሰመራ ከተማ ለሦስት ቀናት የተካሄደው የምክር ቤቱ 6ኛ የምርጫ ዘመን፣ 5ኛ የሥራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባዔ የዳኞችንም ሹመት አጽድቋል።   የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደረሳ መሐመድ በጉባዔው ተገኝተው የክልሉን የ2019 ረቂቅ በጀት ያቀረቡ ሲሆን፣ በጀቱ ከመንግሥት ድጎማ፣ ከክልሉ የውስጥ ገቢ፣ ከፌዴራል መንግሥት እና ከተለያዩ የገቢ አማራጮች የሚሸፈን መሆኑን አንስተዋል። ለበጀት ዓመቱ የተመደበው ገንዘብ የክልሉን ልማት ለማቀላጠፍና የሕዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል ከመሆኑም በላይ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ይረዳል ብለዋል። 4. የኢንቨስትመንት መድረክ ሌላው የሳምንቱ ዓበይት ጉዳይ የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈጻሚ አካላት በጋምቤላ ከተማ ያካሄዱት የጋራ የምክክር መድረክ ነበር። በመድረኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የኢንቨስትመንት እድሎችን በማስተዋወቅና ቀልጣፋ የአሰራር ስርዓቶችን በመተግበር በርካታ ባለሀብቶችን ወደ ሀገር ውስጥ ለመሳብ መቻሉም ተገልጿል።   በመድረኩም ሀገሪቱ ያሏትን የኢንቨስትመንት እድሎች ለባለሀብቶች የማስተዋወቅ እና አገልግሎቶችን ቀልጣፋ ለማድረግ የተሰሩ ሥራዎች ውጤት ማምጣታቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል። የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዳጋቶ ኩምቤ በመድረኩ እንደገለጹት የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ አልሚዎችን ለመሳብ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ ነው። በዚህም በበጀት ዓመቱ ብቻ 528 የውጭ ሀገር ባለሀብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን በማሳያነት አንስተዋል። 5. የወጣቶች ተሳትፎ የላቀበት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በየአካባቢው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው የተገለጸው በዚሁ ሳምንት ነበር። በጅማ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካሞች ቤት ዕድሳት እና ሌሎች የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎችን ለማከናወን በተዘጋጀ መርሃ ግብር ላይ የአቅመ ደካማ ወገኖችን ሕይወት በዘላቂነት ለመቀየር ያለመ ድጋፍ ተደርጓል። ከድጋፎቹ መካከል የትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ፣ የምግብ ግብዓት፣ የንብ ቀፎዎች እና ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ምጣድ ይገኙበታል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ረሂማ ዩሱፍ፣ በክልሉ በርካቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውንና በአገልግሎቱም የወጣቶች ተሳትፎ የላቀ መሆኑን ተናግረዋል። የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ በተያዘው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በዞኑ ከ5 ሺህ 500 በላይ አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤትን ለማደስ መታቀዱንና እስካሁንም ከግማሽ በላይ የሚሆኑት መታደሳቸውን አንስተዋል። 6. ሚኒስቴር ተቋማቱ በበጎ ፈቃድ ተግባር ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አቅመ ደካማ ለሆኑ ወገኖች ልጆች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ያደረገውም በዚህ ሳምንት ነበር። ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን እንደገለጹት፤ ድጋፉ የተደረገው በሐረር ወላጆቻቸው አቅም ለሌላቸው 600 ተማሪዎች ነው። ሚኒስትር ዴኤታው ከሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ዑመር ጋር በመሆን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ያከናወኑ ሲሆን፣ በክልሉ የአቅመ ደካማ ዜጎች መኖሪያ ቤት ግንባታንም አስጀምረዋል። ሚኒስቴሩም ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ክልሎች መሰል የልማት ሥራዎችን በማከናወን ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን አስታውሰዋል።   በተመሳሳይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ በተያዘው ሳምንት ነበር በዱብቲ ወረዳ አሮላፍና ገበላይቱ ቀበሌ የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤቶች ግንባታና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ያከናወኑት። በዚህ ወቅትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታው አምባሳደር ብርሐኑ ጸጋዬ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በተቀናጀ መልኩ ማከናወኑ ማህበራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስቴሩም በዘንድሮው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በአፋር ክልል 10 የአቅመ ደካማ ወገኖች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እያከናወነ መሆኑን አንስተው፣ በተጨማሪም አንድ የቅድመ መደበኛ መዋዕለ ሕፃናት ትምህርት ቤት እንደሚገነባም ነው የገለጹት። 7. የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ውጤታማነት ሳምንቱ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማነት ማሳደጉ የተገለጸበትም ነበር። የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ መንግሥት በተለይ የመሬት፣ የኤሌክትሪክ፣ የፋይናንስ፣ የመሠረተ ልማት እና ሌሎች ጥያቄዎች በአፋጣኝ እንዲመለሱ መደረጉ ኢንዱስትሪዎቹ ውጤታማ እንዲሆኑ አስችሏል ብለዋል።   በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ 11 ከፍተኛ እና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ በመግባት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል። ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ የወጪ ምርቶችን አምርተው በመላክ ለሀገር የውጭ ምንዛሬ እያስገኙ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ጉብኝት ከተደረገባቸው አምራች ኢንዱስትሪዎች መካከል የፈሳሽና ጠጣር ሳሙና፣ የጭማቂ፣ የውሃ፣ የሮቶ፣ የካርቶንና የእርሻ መሳሪያ ማምረቻዎች እንዲሁም የቡና ማቀነባበሪያዎች ይገኙበታል። 8. ሠራዊቱ ከወገን አለኝታነቱ ባሻገር የልማት አጋርነቱን አጠናክሯል ከሳምንቱ ዓበይት ጉዳዮች መካከል የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ዳር ድንበር የማስከበር ግዳጁን ከመወጣት ጎን ለጎን የወገን አለኝታነቱንና የልማት አጋርነቱን የሚያጠናክሩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑም በዋነኝነት የተገለጸበት ነው። በሀገር መከላከያ ሠራዊት የ11ኛ ዕዝ አመራሮችና የሰሜን ወሎ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በቆቦ ከተማ እየተካሄደ ያለውን የኮሪደር ልማት ጎብኝተዋል። የ11ኛ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አድማሱ ዓለሙ በወቅቱ እንዳሉት፤ የቆቦ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቅ ዕዙ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል። በዚህም የዕዙ አመራሮችና አባላት የኮሪደር ልማቱን ለማፋጠን የወር ደመወዛቸውን 40 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።   ድጋፉም ሠራዊቱ የአካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ለልማት ሥራው ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር ባሻገር የወገን አለኝታነቱን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። የዕዙ አመራሮችና አባላት ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡት የቆቦ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኃይለዓብ ወንድሙ፣ ድጋፉ አሁን ላይ 43 በመቶ የደረሰውን የኮሪደር ልማት ፈጥኖ በማጠናቀቅ ለህዝብ አገልግሎት ለማብቃት ያስችላል ብለዋል። 9. ኢትዮጵያን በመገንባት ረገድ የወጣቱ ሚና ወጣቱ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ሁለንተናዊ ተሳትፎውን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ያሳሰቡትም በዚሁ ሳምንት ነበር።   ከንቲባው ይህን ያሳሰቡት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ27ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ23ኛ ጊዜ በድሬዳዋ በተከበረው ዓለም አቀፉ የወጣቶች ቀን ላይ ተገኝተው ነው። በመልእክታቸውም ወጣቶች የተሻለች ሀገርን ለመገንባትና ለመረከብ እያደረጉት ያለው ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት አበረታች ውጤት እየተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። ወጣቶች በተለይም የውሳኔ ሰጪነት ሚናቸውን ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ሀገር ተረካቢ የሆነውን ትውልድ ወደ ላቀ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እንደሚያሸጋግርም በመድረኩ ተገልጿል። 10. ዲጂታላይዜሽንን ለሙስና መከላከል የመደመር መንግሥት የፈጠራቸውን መልካም እድሎች በመጠቀም ለሀገር ልማት በጋራ መትጋትና ልሹ አሰራሮችን መዋጋት እንደሚገባ የተገለጸው በተያዘው ሳምንት ነው። የፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓል ማጠቃለያ መድረክ "የፀረ-ሙስና ትግል ትናንት፣ ዛሬ እና ነገ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዳማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቴ አለነ፤ በሙስና ትግል የመጀመሪያ ምዕራፍ መከላከልን፣ ምርመራንና ክስን በአንድ ተቋም በማድረግ ይሰራ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም እንቅስቃሴው ህዝብን የትግሉ ባለቤት ያላደረገ፣ የሙስና መከላከል ስራን የረሳ እና ለትውልድ የስነ-ምግባር ግንባታ ቦታ የማይሰጥ ነበር ብለዋል።   በሁለተኛው ምዕራፍ፣ ከሚሊኒየም መባቻ ጀምሮ ለውጡ እስከመጣበት ጊዜ ድረስ የነበረው ወቅት በልማታዊ መንግሥት ስም ከፍተኛ ጣልቃገብነት የተካሄደበት እንዲሁም ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ የተስፋፋበት እንደነበር አንስተዋል። በዚህም ምክንያት የህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ ሜጋ የመንግሥት ፕሮጀክቶች በሙስና እና በሌብነት ምክንያት ለከፍተኛ ችግር ተዳርገው እንደነበር አስታውሰዋል። በሦስተኛው ምዕራፍ፣ ከሀገራዊ ለውጡ መባቻ ጀምሮ እስካሁን ባለው ጊዜ ከሙስና ትግል አኳያ መሰረታዊ ለውጥ ተደርጓል ብለዋል። በኮሚሽኑ ላይ ከተደረጉት ማሻሻያዎች መካከል ዋነኛው የሕግ ሪፎርም መሆኑን አንስተው፤ ሙስናን በአንድ ተቋም ብቻ መታገል ስለማይቻል ሁሉም የመንግሥት ተቋማት የትግሉ ባለቤት እንዲሆኑ መደረጉን አስታውቀዋል። በተለይም የዲጂታላይዜሽንን መልካም እድሎች በመጠቀም አገልግሎቶችን ከሰው ንክኪ ነፃ እና አካታች በሆነ መንገድ ማቅረብ መቻሉና መሰረታዊ የእሳቤ ለውጥ ማምጣቱ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ጠንካራ መሰረት እየጣለ መሆኑን አክለው ገልጸዋል። 11. ኢዜአ በበጎ ፈቃድ ተግባር ላይ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ባደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደሰታቸውን በባህር ዳር ከተማ ድጋፍ የተደረገላቸው ተማሪዎችና ወላጆች መግለጻቸው የተዘገበውም በሳምንቱ ነበር።   በወቅቱም የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተፈራ በቀለ፤ ኢዜአ ከመረጃ ተደራሽነት ባሻገር በማህበራዊ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ አገልግሎት በስፋት እየተሳተፈ መሆኑን ገልጸዋል። ኢዜአ የትምህርት ቤቶች ድጋፍ ላለፉት ስድስት እና ሰባት ዓመታት በተከታታይ ሲያከናውን መቆየቱን አንስተው፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ በትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍና በመሰል በጎ ተግባራት ተሳትፎውን አጠናክሮ መቀጠሉንም አክለዋል። በበባሕር ዳር ከተማ የአረንጓዴ አሻራን ከማኖር ባለፈ ኢዜአ ለ357 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉንም ገልጸዋል። የባሕር ዳር ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አስራቴ ሙጨ በበኩላቸው፤ የኢዜአ አርዓያነት ያለው ተግባር በሌሎችም ዘንድ መቀጠል ያለበት መሆኑን ገልጸው፤ ለተደረገው መልካም ተግባር ሁሉ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ስም ምስጋና አቅርበዋል። ድጋፍ የተደረገላቸው ተማሪዎችና ወላጆች ኢዜአ ባደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸው ለተደረገውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ ከትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በተጨማሪ በባህርዳር የመዋዕለ ሕፃናት ትምህርት ቤት የሕንፃ ግንባታን አስጀምሯል። የሚገነባው የመማሪያ ክፍል ለታዳጊ ተማሪዎች ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል ሲሉ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ የገለጹትም በዚህ ወቅት ነው።   የኢዜአ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ምንይችል ዓለማየሁ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ በገጽታ ግንባታ ሥራዎች እንዲሁም የጋራና አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሀገራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።ተቋሙ ከሀገራዊ ተልዕኮው ባሻገር በማኅበራዊ ተሳትፎና የበጎ ፈቃድ ተግባራት ላይም ሰፊ ተሳትፎ በማድረግ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። ኢዜአ በባሕር ዳር ከተማ ምስራቀ ፀሐይ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቅድመ መደበኛ ትምህርት አስተባባሪ መምህርት አያል እምቢያለ፤ በአሁኑ ወቅት በአንድ ክፍል ውስጥ እስከ 150 ተማሪዎች እንደሚማሩ አስታውሰዋል። አዲሱ የመማሪያ ሕንፃ ግንባታ ይህንን የተማሪዎች የክፍል ጥምርታ በማስተካከል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል። ከዚሁ መርሃ ግብር በተጓዳኝም የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀንን ምክንያት በማድረግም ከወጣቶች ጋር የፓናል ውይይት ተካሂዷል።              
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር!
Aug 9, 2026 841
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር! በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን ) የገጠሩ ማህበረሰብ የጨለማ ኑሮ የተፈረደበት ይመስል ኑሮውን ማሻሻል ሳይችል እልፍ ዓመታት ተቆጥረዋል፤ ለዘመናት መብራትና ውኃ ለማግኘትና ከቴክኖሎጂ ጋር ተቀራርቦ ለመኖር ወደ ከተማ መሰደድ ብቸኛው አማራጭም ነበር። የከተሜው ዋልታ የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት የሚወሰንበት የአራሹ ገበሬ የኑሮ ደረጃ ባህላዊውን የአኗኗር ዘዬ ባለመልቀቁ ደስተኛ ጊዜ የሚያሳልፍበት ሂደት አድካሚ እንደሚሆን ግልጽ ነው። የገጠሬው የተበታተነ የአኗኗር ሥርዓትም ለገጠሬው አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፤ የእዚህን የህብረተሰብ ክፍል ምርቱን እንጂ ኑሮውን የጠየቀ አልነበረም ቢባል ግነት አይሆንም።   ቀደም ሲል በነበሩ መንግስታት ከተማን እንጂ ገጠርን ማዘመን የሚያስብ ስለመኖሩ ያጠራጥራል፤ ይህም በሀገሪቱ ለኢፍትሐዊ ዕድገት የራሱን ተጽዕኖ ሲያሳደር ቆይቷል። የመደመር መንግሥት ግን ይህን ቀይሮታል። ሀገር የመምራት ኃላፊነት ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ በከተማና በገጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ በዜጎች የኑሮ ሥርዓት ላይ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርጎ እየሰራ ነው ከተሜነት ብቻውን አድጎ የገጠሩ ማኅበረሰብ በቀድሞ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሆነ የተሟላ ዕድገት ማምጣት አይቻልም የሚል ጽኑ እምነት አለው። በእዚህም ከተማና ገጠርን ለማቀራረብ በገጠር ትራንስፎርሜሽንን የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ቀርጾ መተግበር ከጀመረ ከራርሟል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን አንዱ አካል የሆነው የገጠር ሞዴል መንደር በአርሶ አደሮች ዘንድ የሚጨበጥ ተስፋን ይዘው ከመጡ ኢኒሼቲቮች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። ከተስፋ ተሻግረው በዚህ ሞዴል መንደር የነዋሪነት ዕድልን ያገኙት ደግሞ ብርሃን አይተዋል፤ የትናት አኗኗራቸውን የቀየረ አዲስ ዛሬን በእጃቸው አድርገዋል፤ ነገን አልቀው መመልከት የግብርና ተግባራቸው አንዱ አካል ሆኗል። በአዲሱ መንደራቸው ዛሬ የሚያፈስ ቤት የለም፣ የእንስሳት ቆሻሻ ሽታ በአፍንጫቸው አይገባም፣ በሚቆረቁር እንጨት ወይም መደብ ላይ አይቀመጡም፤ የከተሜው መዘነጫ ሶፋ በሳሎናቸው ተከስቷል። ጓሮዎቻቸው ሁሉ ሙሉ እንደሆኑ አፍ አውጥተው የሚያወሩ ናቸው። በዚህ ቆስጣ፤ በዛ በኩል ጎመንና ቀይስር፤ ዘውር ሲሉ ደግሞ ከአስር የሚልቁ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፤ በአንድ ክፍል ደግሞ እናት ላም ከጥጃዋ ጋራ፣ የእንቁላል ዶሮ ከሥጋ ዶሮ ጋር ሁሉንም በአንድ ጊቢ ውስጥ ያገኛሉ። ምን ይሄ ብቻ አቮካዶ እና ፓፓያ፣ ሙዝና እንሰት፣ በርበሬና ሽንኩርት ሳይቀር ለተትረፈረፈ የአርሶ አደር ማዕድና ገበያ ራሳቸውን አዘጋጅተዋል።   አርሶ አደር ኃይሉ ሞትንሞስ በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ ናቸው። እርሳቸው "መንግስት ጨለማችንን ገፎ ብርሃን አሳየን" ሲሉ በጠንካራ ቃላት የገጠር ሞዴል መንደር ፕሮጀክት ያመጣላቸውን በጎ ነገር ይገልጻሉ። እውነት ነው ያላዩትን ብዙ ነገር አሳይቷቸዋል። ያም ብርሃን ቤት ውስጥ የሚበራ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው፣ በነገ ተስፋቸውና በኢኮኖሚያቸው ላይ የፈነጠቀ ብርሃን ነው። ዛሬ ያሉበትን ህይወትም "ለእኔ አዲስ ነገር ነው። አይቼው አላውቅም፤ መቼም በራሴ ሀሳብ አላደርገውም ነበር።" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግስት አበራልኝ ያልኩት በእጄ ያለኝን ያላየሁትን ዕድል ስላሳየኝ ነው በማለትም ሀሳባቸውን ይቀጥላሉ። እኛ ሀብት አለን፤ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም። ይልቁንም የምናባክነው ይበዛል በማለትም የቀደመ ሕይወታቸውን እያሰቡ ይቆጫሉ። አሁን ግን ብዙ ተገነዘብኩ የሚያስብል የመደመር መንግስት በመኖሩ አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። እርግጥ ነው የገጠር ሞዴል መንደር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ነው። ለአብነትም የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ማንሳት ይቻላል። የተሠሩ ሞዴል መንደሮች በመጀመሪያ የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ የመሆን ዕድል ገጥሟቸዋል። በመቀጠል ንጽሕናው ያልተረጋገጠ የመጠጥ ውኃ ወንዝ ወርዶ ከመቅዳት ተቆጥበው በመንደራቸው የተገነባውን የከረሰ ምንድር ውሃ ከቧንቧ ቀድተው መጠጣት አስችሏቸዋል። በእሳት እና ኩራዝ ጭስ ሲሰቃዩ የነበሩ ዓይኖቻቸው ዛሬ ከሶላር ቴክኖሎጂ የመነጨ ብርሃን ማየት ጀምረዋል። ብርሃን ብቻ አይደለም ለወትሮ ለገበያ ወደ ከተማ ብቻ ሲወጡ ይመለከቱ የነበረውን ቴሌቪዥን ዛሬ በቤታቸው አስገብተው የመረጃና የመዝናኛ ዓለምን ተቀላቅለዋል። አርሶ አደሮቹ ቴሌቭዥንን ከመዝናኛነት ይበልጥ ለመረጃ እንደሚጠቀሙት ያነሳሉ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በዜና ተከታትሎ መረዳት፣ የገበያ ሁኔታን ማወቅ፣ የግብርና ሥራ ተሞክሮን መቅሰምና የአየር ንብረት ሁኔታን ጨምሮ ለሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙት ከቴሎቪዥን መስኮት እንደሆነ ይናገራሉ።   በጓሯቸው የተትረፈረፈ የሌማት ትሩፋት ምርት መሰብሰብ የሚያስችላቸው ምቹ ሁኔታ ደግሞ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው። በተለይ መንግስት በጓሯቸው ጥምር እርሻ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የነገ ኢኮኖሚያቸውን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ ነው። ከተማን መናፈቅን ያስቀረው የገጠር ሞዴል መንደር ያኔ ከጅምሩ አመኔታን አላገኘም። የቦታና የአካባቢ ቁሳቁስ ለማቅረብ ዝግጁ እስካለመሆን የደረሱ አርሶ አደሮችም ነበሩ። በወቅቱ ጉዳዩን እንደፌዝ አዩት። ዛሬ ግን ውጤቱን በአግራሞት በዐይናቸው ተመለከቱ። የተናገረውን የሚከውን፤ የጀመረውን የሚጨርስ የመደመር መንግሥትን ተጨባጭ ስራዎች በማረጋገጥ እንደ ትንግርት ቆጠሩ። ዛሬ በየአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በቁጭት ተሞልተው መንደራቸውን ወደዚህ የሞዴል መንደር እሳቤ ለመቀየር ተነሳስተዋል። የጌሊት ቀበሌ አርሶ አደሮቹ መኮንን አርዶ እና ነጻነት ተስፋሁን ለዚህ ተጠቃሾች ናቸው። ያዩትን ተሞክሮ በራስ አቅም በመንደራቸው ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ከተማ ሄደን የምናወጣውን ወጪና የምናባክነውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት እዚሁ መዝናናት የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል።   "ይህ ዕድል ለእኛ ለአርሶ አደሮች በታሪክ የሚነገር ትልቅ አጋጣሚ ነውም" ይላሉ። በጤዛ እየራስን እንጓዝበት የነበረው መንገዳችን ዛሬ ሰፍቷል። ተሽከርካሪ በደጃችን ስለሚያልፍም ምቹ ዕድልን ይዞልን መጥቷል። ይህን ጅምር ተግባር ወደ ላቀ ውጤት ማሸጋገር የእኛ ድርሻ ነውና ጠንክረን እንሠራለንም ብለዋል።   ይህን ዕድል ወደ ትልቅ አቅም ለመቀየር መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ የሸሸቃ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር አልዓዛር ዘርክናንስ ናቸው። የዶሮና የከበት እርባታን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ ሥራን ከመደበኛው የእርሻ ሥራ ጋር አስተሳስረው በመሥራት ከቤተሰብ ፍጆታ ተርፎ ለገበያ የሚበቃ ምርት ለማምረት እየተዘጋጁ ነው።   ይህም የገቢ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ልጆቻቸው ወተትና የወተት ተዋጽኦ በቤታቸው እንዲያገኙ ያደርጋል። ማር፣ እንቁላል እና ሥጋ እንዳያምራቸው የሚያደርግ ትልቅ ኢኒሼቲቭም ነው። አንዱ ቢጎድል በሌላው እየሞሉ የሚኖሩበትን የሥራ መስክ አጠናክረው ለውጤት አብቅተው ለተሻለ ለውጥ እንደሚሠሩ አክለዋል። የአርሶ አደር እናቶች ዘምቢል ይዘው አትክልትና ፍራፍሬ ሸመታ ወደ ገበያ ማቅናት የለባቸውም። ይልቁንም ከጎሮቸው ወደ ገበያ ይዞ መውጣት የኑሮ ዘዬያቸው ወግ ነው። ወይዘሮ መሠረት ማሞ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ያልለመዱትን አዲስ ሕይወት ከአዲስ ተስፋ ጋር መጀመራቸውን ከሚናገሩት መካከል ናቸው።   ትናንት ኩሽናቸው፣ መኝታቸው እንዲሁም የከብትና የዶሮ ማደሪያ በአንድ ቤት ወስጥ የተወሰነ እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን ሽንት ቤትና መታጠቢያ ቤት ሳይቀር ለየብቻ የራሱ የሆነ ቤት ተገንብቶ ጽዳቱ የተጠበቀ ኑሮ መኖር ጀምረዋል። ቤታቸው ሲገቡና ሲወጡ ለዓይን ማራኪ፤ ለመቀመጥ ምቹ፤ ለመተኛትም ንጹህና ወገብ የሚያሳርፍ ሆኖ አግኝተዋል። እናም በዚህ እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። "መንግስት እንደ አባት ጎዶሏችንን ሞልቷል" ሲሉም ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ የአርሶ አደሮችን ሕይወት ብሩህ ያደረገው የገጠር ሞዴል መንደር ኢኒሼቲቭ በመላው ሀገሪቱ በመስፋፋት ላይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 16 ሞዴል መንደሮች በ16 ወረዳዎች ተገንብተዋል።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ኢኒሺዬቲቩ የአርሶ አደር ኑሮ ዘዬን ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ጋር ለማቆራኘት ያስቻለ ነው። የተሻለ መኖሪያ ቤት ኖሮት በጓሮው የሚበላ ነገር ካጣ ሕይወቱ ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም። ይህም በመሆኑ ቤቶቹን ከእያንዳንዱ የግብርና ልማት ዘርፎች ጋር በማጣመር እንዲገነቡ የተደረገው። ይህም የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ስትራቴጂን የሚያጠናክርና ገበያን የማረጋጋት ዓላማን የያዘ ጭምር ነው። በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ የተገኘው መልካም ውጤት በቀጣይ በሁሉም ወረዳዎች የሚስፋፋ ሲሆን በዞን እና ወረዳ መዋቅሮች ድጋፍና ክትትል በቀበሌ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አንስተዋል። ይህ ኢኒሼቲቭ የሀገራዊ ብልጽግና ጉዞ አንዱ አቅም ነው። የተደመረ የማኅበረሰብ ብልጽግና ሀገርን ከፍ ያለ የዕድገት ማማ ላይ ያስቀምጣታል። እነሆ የክልሉ አርሶ አደሮች የአካባቢያቸውን ጸጋ ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ የሚቀይሩበት መስክ በሞዴል መንደር ምክንያት እጃቸው ላይ ደርሷል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉትም በብዙ መንገድ ጨለማ የከበበው የገጠሩ ማኅበረሰብ ሕይወት ዛሬ ብርሃን ማየት ጀምሯል። ይህ የብርሃን ፋና እየተቀጣጠለ ወደ ብዙኃኑ ሊደርስ የሁሉንም ፍላጎት አነሳስቷል። ሥሩ ከማለት ይልቅ ሠርቶ ማሳየትን የሚያስቀድመው የመደመር መንግስት የፈጠራቸው የገጠር ሞዴል መንደሮች ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን በዘላቂነት የሚያሳምሩ ናቸው። ሰላም እንሰንብት!  
ትንታኔዎች
የግብጽ እኩይ ሴራ የማይገታው የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት መብት
Aug 19, 2026 175
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች የምትገኘው እና የቀጣናው የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋት ዋና መሠረት ነች። የኢትዮጵያ፣ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የፖለቲካ ፍላጎት ሳይሆን ሀገራዊ ሕልውናንና ደህንነትን የማረጋገጥ፣ የልማትና ብልጽግናን ዕውን የማድረግ የትውልድ ጥያቄ ነው። ትልቅ አቅም ያላት ኢትዮጵያ በመልክዐ-ምድራዊ እስር ውስጥ እንድትቀር የሚደረገው ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍትሕን የሚቃረን አካሄድን ለማረም ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት የነበራት የባህር በር ባለቤትነት እና የማሪታይም መብት በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እየሰራች ነው። ይህ የኢትዮጵያ ፍትሐዊና የማይቀረው የሕልውና ጥያቄ በዓለም አቀፉ የባሕር ሕግ ኮንቬንሽን (UNCLOS) የተረጋገጠ እና በጋራ ተጠቃሚነት (Win-Win) መርሕ ላይ የተመሠረተ ቢሆንም፣ የግብጽ ፖሊሲ አውጪዎች ግን ይህንን የሕልውና ጥያቄ ለማክሸፍ የሴራ እና የከበባ ስትራቴጂያቸውን ለማስፈጸም እየሰሩ ይገኛሉ። የግብጽ ሴራ በዋናነት ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ለወደብ ኪራይ እንድታወጣ በማስገደድ፣ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት የሚወጣው ካፒታል እንዲሟጠጥ በማድረግ የሀገሪቱን የኢንዱስትሪያላይዜሽንና የልማት ዕድገት ለማቀጨጭ ያለመ የኢኮኖሚ ዘመቻ ነው። በተጨማሪም ግብጽ የቀይ ባሕርን ማሪታይም ቀጣና “የባሕር ዳርቻ ሀገራት ብቻ (Littoral States) ይዞታ" አድርጋ በመሳል፣ የኢትዮጵያን ታሪካዊና ሕጋዊ የመጠቀም መብት በመካድ ከማንኛውም የቀይ ባሕር የደህንነትና የኢኮኖሚ ስብስብ እንድትገለል እየሰራች ትገኛለች። ግብጽ ከኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርጋቸው ወታደራዊ ስምምነቶች በሰሜንና በምሥራቅ ድንበሮች አካባቢ አዲስ የደህንነት ስጋት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ ሀብቷንና ትኩረቷን ወደ የብስ ጥበቃ እንድታዞርና ለባህር ኃይል ግንባታ የምታውለውን አቅም እንድታበታትን የታለመ የከበባ ስልትም ነው። በዓለም አቀፍ የፋይናንስና የኢንቨስትመንት ተቋማት ዘንድ የምታደርገው የዲፕሎማሲ ጫና፣ ኢትዮጵያ ለወደብ እና ለትራንስፖርት ኮሪደሮች ልማት የሚሆን የውጭ ኢንቨስትመንት እንዳታገኝ እና የቀይ ባሕር አካባቢ የስጋት ቀጠና ተደርጎ እንዲቆጠር በማድረግ ኢንቨስተሮች እንዲሸሹ በማድረግ ላይ ናት። በጎረቤት ሀገራት ዘንድ የጥርጣሬ እና የስጋት ግንብ በመገንባት፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር የምታደርጋቸው ፍትሐዊና የጋራ ዕድገትን ያለሙ የወደብ ስምምነቶች የሉዓላዊነት መጣስ ተደርገው እንዲቆጠሩ የማስፈራራትና የሐሰት ትረካና ዘመቻ ታካሂዳለች። ግብጽ የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት ላይ አንድ ወጥ አቋም እንዳይዙ ለማድረግ ድርጅቶቹን የፖለቲካ ፍልሚያ መድረክ በማድረግ የቀጣናውን ተቋማዊ ትብብር የማደናቀፍ ተግባር እያከናወነች ይገኛል። የግብጽ ሚዲያዎች የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ የ130 ሚሊዮን ሕዝብ የረጅም ጊዜ ሕልውና እና የትውልድ ጥያቄ መሆኑ እየታወቀ ጠባብ የፖለቲካ አጀንዳ በማስመሰል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲይዝ የማድረግ ስራ ላይ ተጠምደዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና (AfCFTA) ውስጥ የምታደርገውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ፣ የወደብ ትራንዚት ወጪዋ ከፍተኛ ሆኖ እንዲቀጥል በማድረግ ምርቶቿ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ጫና ለመፍጠር ትሰራለች። የግብጽ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን ለዘለቄታው የመልክዐ-ምድር እስረኛ አድርጎ በማስቀረት፣ በምሥራቅ አፍሪካ የሚኖራትን ጂኦ-ፖለቲካዊና የኢኮኖሚ የበላይነት መግታት ነው። ሆኖም የግብጽ ሴራ የኢትዮጵያን የልማት መንገድ ሊያስቆመው አይችልም። ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በሕዝቦቿ የማይበገር ጽናትና ቁርጠኝነት እውን እንደሆነ ሁሉ፤ በቀይ ባህር ላይ ህጋዊና ፍትሃዊ መብትን የማረጋገጥ ጉዞም የቀጣናውን የታሪክ ሂደት የሚቀይር የማይቀለበስ ብሔራዊ የህልውና ጉዳይ ነው።
መደመር የደረመሠው የጠላት ካምፕና የባንዳዎች እሪታ
Aug 19, 2026 304
በምስራቅ አፍሪካና በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የካይሮ እጅ ሁልጊዜም ኢትዮጵያን ማዕከል ያደረጉ እኩይ ስትራቴጂዎችን በመተለም ይታወቃል። የዓባይ ወንዝ ዋነኛ ምንጭና የተፈጥሮ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያን ማዳከም፣ የውስጥ ግጭቶችን ማበረታት እና በቀይ ባሕር እንዲሁም በኤደን ባሕረ-ሰላጤ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍላጎት ማደናቀፍ የግብፅ የረጅም ጊዜ የውጭ ፖሊሲ መሠረት ሆኖ ቆይቷል። ግብፅ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በወታደራዊ ኃይል ኢትዮጵያን በግልጽ ወርራ ለመቆጣጠር ባደረገችው ሙከራ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1875 በጉንደት እንዲሁም 1876 በጉራዕ ጦርነቶች በኢትዮጵያ አሳፋሪ ሽንፈት አስተናግዳለች ። ከዚህ የቀጥታ ወታደራዊ ሽንፈት በኋላ ካይሮ ኢትዮጵያን በግልጽ ጦርነት ማንበርከክ እንደማትችል ተረድታ ወደ ተዘዋዋሪ የውስጥ ሴራና የእጅ-አዙር ጦርነት ተሸጋግራለች። ካይሮ ኢትዮጵያ ጠንካራና የበለፀገች ሀገር ሆና ከተነሳች በዓባይ ውሃ ላይ ያላትን አጠቃላይ የበላይነት እንደምታጣ ስለሚሰማት፣ የሀገሪቱን እድገት የማደናቀፍና በጂኦፖለቲካው መስክ ወደብ አልባ አድርጎ የመዝጋት ስትራቴጂን ለዘመናት ስትከተል ኖራለች። ይህም የታሪክ እውነታ ከትላንት እስከ ዛሬ በስውርና በግልጽ የሴራ መረቦች ተሸርቦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሲፈታተን የኖረ መራራ እውነት ነው። የቡትሮስ ብትሮስ ጋሊ የዲፕሎማሲ ሽፋን እና ኢትዮጵያን ወደብ የማሳጣት ሴራ በታሪክ አጋጣሚዎች እንደምናየው፣ በግብፅ የፖለቲካ ልሂቃን የታቀዱ ሴራዎች በዓለም አቀፍ መድረኮች እንዴት ተግባራዊ እንደሆኑ አንደኛው ማሳያ የቀድሞው ግብፃዊ ዲፕሎማት ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ አካሄድ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በ1970ዎቹ መጨረሻ በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራር በነበሩበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ በውስጥ ግጭት እንድትታመስና የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ ስጋት እንዳትሆን ከበስተጀርባ የዓመፅ ኃይሎችን የማጠናከር ስራ ሲሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ሃቅ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በውሃ ፖለቲካ ረገድ በሰጡት የታወቀ ንግግራቸው “ቀጣዩ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና የሚካሄደው ጦርነት በፖለቲካ ምክንያት ሳይሆን በውሃ ምክንያት የሚደረግ ይሆናል” በማለት ለቀጣናው ያሰቡ መስለው የካይሮን የውሃ የበላይነት ስጋትና ፍላጎት በግልጽ አንጸባርቀው ነበር። ይህ ንግግራቸው ግብፅ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት የመቆጣጠር ፍላጎቷንና ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ የልማት ፕሮጀክቶችን እንዳታካሂድ ለማድረግ የምታደርገው ሴራ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲያገኝ ዓላማ ያደረገ አደገኛ ንግግር ነው። በኋላም እ.ኤ.አ በ1993 ኤርትራን ከኢትዮጵያ በመገንጠል ሂደት ውስጥ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የስድስተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ ነበሩ። በወቅቱ 99 ነጥብ 8% የሚሆኑት ኤርትራዊያን በሕዝበ ውሳኔ ነጻ ሀገርንትን መርጠዋል በሚል ሕወሃትና ሻዕቢያ የሰሩት ድራማ ተቀባይነት አንዲያገኝ የተመድ ዋና ጸሐፊው ከፍተኛ ሴራ ሰርተዋል። ይህ የኤርትራ ህዝብን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በሻዕቢያ ባርነትና ግዞት እንዲማቅቅ ያደረገው የሕዝበ ውሳኔ ድራማ ላይ ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊ የመሪ ተዋናይነትን ሚና ተጫውተዋል። በሂደቱም ዋነኛ ዓላማቸው የሆነውን ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በሯን እንድታጣ አድርገዋል። ይህም የካይሮ የረጅም ጊዜ “ኢትዮጵያን የመዝጋት” ስትራቴጂ አካል እንደነበር ግልጽ ነው። የካይሮ መጥረቢያ እና አሁናዊው የጥፋት መንገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት የመጥረቢያ ተምሳሌታዊ ማብራሪያ፣ ሕገ ወጡ ሕወሃትን እንደ መጥረቢያ ብረት፤ ሻዕቢያን ደግሞ እንደ መጥረቢያ ዛቢያ ያስቀመጡ ሲሆን፤ መጥረቢያውን የሚያዘውና የሚወረውረው ሌላ ሶስተኛ አካል መኖሩንም ተናግረዋል። እንደሚታወቀው መጥረቢያ አንድን ነገር የመቁረጥና የማፍረስ ስራ ለማከናወን የሶስት አካላት ቅንጅት ያስፈልገዋል፦ ወርዋሪው (እጁ)፣ ዛቢያው (መያዣው) እና ብረቱ (ቁራጩ)። በዚህ ተምሳሌት ውስጥ ወርዋሪው ወይም መጥረቢያውን ጨብጦ ስራ ላይ የሚያውለው አካል ግብፅ ናት። ወርዋሪው ሁልጊዜም ከበስተጀርባ ሆኖ ስትራቴጂ ይነድፋል፣ ፋይናንስና ወታደራዊ ድጋፍ ያቀርባል፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሽፋን ይሰጣል። በሌላ በኩል የመጥረቢያ ብረት ያለ ዛቢያው (መያዣው) ኃይል አግኝቶ ማረፍ አይችልም፤ ዛቢያውም ያለ ወርዋሪው እጅ መንቀሳቀስ አይችልም። በዚህ ሂደት ሻዕቢያ (እንደ ዛቢያ) በቀጣናው ውስጥ የካይሮን ፍላጎት ለማስፈጸም የመያዣነት ሚና ይጫወታል። ቀጣናውን ለማተራመስ በሞመከር የካይሮን ስትራቴጂካዊ ፍላጎት ለማሳካት መንገድ ይከፍታል። ህገ-ወጡ ህወሓት ደግሞ እንደ መጥረቢያ ብረት በሀገር ውስጥ ሆኖ የሀገሪቱን መዋቅር፣ የህዝቦችን አንድነት እና ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ጥቅም ለመሸርሸር የሚሰራ ተላላኪ መሳሪያ ነው። በዚህ የሴራ ትስስር አሁን ላይ ኢትዮጵያ በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት ማደናቀፍ ዋነኛ ዓላማው አድርጎም እየሰራ ይገኛል። ግብፅ “የቀይ ባሕርና የኤደን ባሕረ-ሰላጤ የባሕር ወሰን ያላቸው ሀገራት ብቻ ናቸው በውሃው ላይ መወሰን ያለባቸው” የሚል መርህ በማንሳት፣ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትንና በቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኘውን ትልቁን ኢኮኖሚ (ኢትዮጵያን) ያገለለ ህገ-ወጥ ስብስብ ለመፍጠር እየሰራች ነው። በተጨማሪም በቅርቡ ከሶማሊያና ከሌሎች የአካባቢው ሀገራት ጋር የተደረጉ የውትድርናና የደህንነት ስምምነቶች፣ የሶማሊያን ሰላም ለማስጠበቅ ሳይሆን ቀጣናውን ለማተራመስና ወታደራዊ ስጋት ለመፍጠር የተቃኙ ናቸው። ይህ ሁሉ አካሄድ ዋነኛ ዓላማው ቀጣናውን የውክልና ጦርነት ማዕከል በማድረግና ኢትዮጵያ ወደ ባሕር እንዳትቀርብ ሆነ ተብሎ የተሰላ ሴራ ነው። ከቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ እስከ ዛሬው የቀይ ባሕር ሴራዎች ድረስ የተዘረጉት መረቦችም ይህንኑ እውነት ያሳያሉ። የካይሮ መጥረቢያዎችን ያዶለዶመው የመደመር መንግሥት ጥንካሬ ግብጽ እያከናወነችው ባለው አሁናዊ ሴራ ውስጥ የካይሮ ስትራቴጂስቶች የሳቱት ትልቅ እውነታ አለ። የግብጽ የሴራ መጥረቢያዎች ለመቁረጥ የሚሞክሩት በፈተናዎች የማትበገረውን እና እንደ ወርቅ በእሳት ውስጥ ተፈትና ያለፈችውን ኢትዮጵያን መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በታሪኳ የውጭ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎችን አሸንፎ መውጣት እንግዳ የሆነባት ሀገር አይደለችም። ባለፉት ክፍለ ዘመናት በወረራ፣ በውስጥ አለመረጋጋትና በጂኦፖለቲካዊ ከበባዎች ውስጥ አልፋ የጸናች ሀገር ናት። ወርቅ በእሳት ውስጥ ሲያልፍ ቆሻሻው ተወግዶ ይበልጥ እንደሚበራ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በተጋረጡባት የህልውና ፈተናዎች ሁሉ አልፋ ይበልጥ እየጠነከረችና እየተደራጀች መምጣቷ የታሪክ እውነታ ነው። አሁን ባለንበት ዘመን ደግሞ ይህ ጥንካሬዋ ይበልጥ ጎልብቷል። የመደመር መንግሥት ቁልፍ ፍልስፍና እና እየተገበራቸው ያሉ እርምጃዎች የካይሮን የረጅም ጊዜ የእጅ አዙር ጦርነትና ሴራዎችን ከንቱ ያደረገ ነው። የመደመር መንግሥት የውጭ ጫናዎችንና ሴራዎችን ለመመከት የመጀመሪያው ምሽግ የውስጥ አቅምን ማጠናከር መሆኑን በመገንዘብ፣ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለፍፃሜ ማብቃትና ግዙፍ የግብርና፣ የአረንጓዴ አሻራ እና የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን እውን አድርጓል። ይህም ግብፅ ኢትዮጵያን በልማት እንዳትበለፅግ ለማድረግ ያቀደችውን ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ አክሽፎታል። ካይሮ ኢትዮጵያን በጂኦፖለቲካዊ ከበባ ለማዳከምና በውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የነደፈችው የረጅም ጊዜ የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት ባስመዘገባቸው የልማትና የዲፕሎማሲ ድሎች ምክንያት ሙሉ በሙሉ ተደርምሷል። ይህ የጠላት ካምፕ መደርመስና የኪሳራ ስሌት ደግሞ በካይሮ ስትራቴጂስቶችና በውስጥ ተላላኪዎቻቸው (ባንዳዎች) ዘንድ ታላቅ ድንጋጤንና ተስፋ የመቁረጥ እሪታን ፈጥሯል። በመሆኑም የተበተነው የጠላት ካምፕና የተበሳጩት ባንዳዎች ብቸኛ አማራጭ አድርገው የያዙት በሳይበርና በሚዲያ ምህዳር የሃሰት መረጃዎችን ማንደድና የፕሮፓጋንዳ ማዕበል መፍጠር ቢሆንም፣ ይህም የተስፋ መቁረጥ ድምፅ ብክለት እንጂ የኢትዮጵያን የጽናት ጉዞ የሚያስተጓጉል አይሆንም። በሌላ በኩል ግብፅ “የቀይ ባሕር ሀገራት ጥምረት” በሚል ስም ቀጣናውን ለማተራመስና እርስ በርስ ጥርጣሬ ለመፍጠር የምታደርገውን የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት የጋራ እድገትና የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በማስቀደም በዲፕሎማሲው መስክ እየመከተው ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ምክክር የጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ በጋራ እንዲወስኑ በማድርግም የካይሮ ስትራቴጂስቶች በኢትዮጵያ የውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የጠነሰሱትን ሴራ ከንቱ አድርጎታል። በአጠቃላይ ታሪክ እንደሚነግረንና የወቅቱ እውነታ እንደሚመሰክረው፣ የግብፅ የሴራ መጥረቢያዎች በፈተናዎች እሳት ተፈትና ባላለፈች ደካማ ሀገር ላይ ያረፉ አይደሉም። ለመቁረጥ የሞከሩት በጽናት፣ በህዝቦቿ መስዋዕትነትና በፅኑ ታሪካዊ መሰረት ላይ የቆመችውን ኢትዮጵያን ነው። አሁን ላይ በመደመር መንግሥት መሪነት እየተገነባ ያለው የውስጥ አቅም፣ የልማት ስኬትና በራስ መተማመን የካይሮን የረጅም ጊዜ የከበባ ሴራ ሙሉ በሙሉ ወድቅ ማድረጉን ቀጥሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ሁሉ አሸንፎ ማለፍ የሰርክ ተግባሯ እንደመሆኑ መጠን፣ የዛሬውንም የጂኦፖለቲካ ውጥረትና የሴራ መረብ በጽናት አልፋ የቀጣናው የልማትና የሰላም ማዕከል ሆና መቀጠሏ የማይቀየር እውነት ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ፦ የምግብ ሉዓላዊነት ምሰሶ
Aug 14, 2026 372
(በሙሴ መለሰ) የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአፈር መሸርሸር እና የተፈጥሮ ሀብቶች መመናመን በአሁኑ ወቅት የዓለማችን ዋነኛ የህልውና ስጋቶች ሆነዋል። ኢትዮጵያም የዚህ ችግር ተጠቂ ናት። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ ተግዳሮቶቹን በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ነው። የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም፣ የደን ሽፋንን መጨመር፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት በወቅቱ አረንጓዴ ዐሻራ ሲጀመር የነበሩ አበይት አላማዎች ናቸው። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ መጀመሩ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘንድሮው ዓመት ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ መቀመጡን እና በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የምታስተናግደው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ድረስ የሀገሪቱን ግብ ወደ 65 ቢሊዮን ከፍ ለማድረግ መታቀዱን ገልጸዋል። ሐምሌ 27/ 2018 በተካሔደው የዘንድሮው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይም 800 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል ታቅዶ፣ 805 ነጥብ3 ሚሊዮን በመትከል ከእቅዱ በላይ ማሳካት ተችሏል። ከ26 ነጥብ2 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው የተሳተፉበት ይሄ መርሃ-ግብር በአጠቃላይ 294 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ነበር። በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ለመትከል ከታቀደው ስምንት ቢሊዮን ችግኞች መካከልም ከ6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ መተከሉን መረጃዎች ያሳያሉ። የአረንጓዴ ዐሻራ ከአካባቢ ጥበቃ ስራ ባሻገር ሀገራዊ የምግብ ዋስትናን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። መርሃ-ግብሩ ከተራቆቱ መሬቶች መልሶ ማገገም ባለፈ፣ በምግብ ራስን ለመቻል እየተደረገ ባለው ጥረት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ ዐሻራ ከተለመደው የደን ልማት በተለየ መልኩ የግብርና ደንን (Agro-forestry) በማስፋፋት የአርሶ አደሩንና የከተማውን ማህበረሰብ የምግብ ፍላጎት በቀጥታ መመለስ ላይም ያተኮረ ነው። እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን፣ ቡና እና ሙዝ ያሉ የምግብና የፍራፍሬ ችግኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ ተተክለዋል። ይህ አካሄድ አርሶ አደሮች ከሰብል ምርት በተጨማሪ ከተተከሉት ዛፎች የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። ከዛም ባለፈ ለገበያ በማቅረብ የሚገኘው ተጨማሪ ገቢም የአርሶ አደሩን አቅም አሳድጎታል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮ አካባቢ ምህዳርን ለመጠበቅ የሚያስችሉ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል። የተተከሉት ችግኞችም ትርጉም ያላቸው የዜጎችን ተጠቃሚነትና የአካባቢ ጥበቃን ታሳቢ ያደረጉ ናቸው። ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚሆነው የጥምር እርሻ ደን ሲሆን 35 በመቶ የሚሆነው ደግሞ የደን ዛፍ ነው። ቀሪው ደግሞ የከተማ ውበት ዛፎች ናቸው። የተተከሉ ዛፎች አፈርን ከውሃ መሸርሸር በመጠበቅና የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጨምር በማድረግ የሰብል ምርታማነትን ያሳድጋሉ፤ እንዲሁም የደረቁ ምንጮችን በማነቃቃት የመስኖ ልማትን ያበረታታሉ። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተከላው ሂደት፣ የንብ እርባታንና የእንስሳት መኖ አቅርቦትን በማሳደግ የዘላቂ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል። በሌላ በኩል፣ ይህ አገራዊ ንቅናቄ በከተማ ግብርና ላይ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በከተሞች ዙሪያ የሚለሙ የፍራፍሬ ችግኞች በአነስተኛ ይዞታዎች ላይ የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ናቸው። ይህ አካሄድ በከተሞች የሚታየውን የምግብ ፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን በመቅረፍ፣ በምግብ ራስን ከመቻል አንጻር የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የሚያደርግ ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገሪቱን የምግብ ዋስትና በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት እና በምግብ ራስን የመቻል አገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚተገበር ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ነው። ንቅናቄው ከተራቆቱ መሬቶች መልሶ ማገገም ባለፈ፣ በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት የሚያፋጥንበትን ሁለንተናዊ አቅም ፈጥሯል። ኢትዮጵያዊያን እንደ አድዋ እና እንደ ህዳሴ ግድብ ሁሉ በአንድ ድምጽ በመደመር እሳቤ በአንድነት ተነስተው በጋራ እየፈጸሙት ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከችግኝ መትከልም በላይ ነው። ይሄ አንድነት ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ የተላቀቀች ለቀጣናው ለአህጉሩና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በአርዓያነት እያስጠቀሳት የሚገኝ ነው። ትውልዱ በየዓመቱ በሚከናወነው በዚህ መርሃ-ግብር ዐሻራውን ከማሳረፍ ባለፈ በእንክብካቤውም የተናበበ ሆኖ መቀጠል የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን የማድረግ መሻቱን ማሳካት ይጠበቅበታል።
ከአረንጓዴ አሻራ እስከ ዓለም ገበያ - የኢትዮጵያ ቡና ልማት አዲስ የዕድገት ምዕራፍ
Aug 13, 2026 514
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቡና መገኛ ከመሆኗም ባለፈ ምርቱ አሁንም ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብትና ማህበራዊ ህይወት ትልቅ መሰረት ያለው ነው። የዓለም የቡና ዝርያዎች ሁሉ መገኛ የሆነው የአረቢካ ቡና ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘውም በኢትዮጵያ እንደሆነ ይታወቃል። በኢትዮጵያ ቡና መጠጣት የዕለት ተዕለት ባህል ሲሆን፣ የቡና አፈላል ስነ ስርዓት ሰላምን፣ አንድነትንና ማህበራዊ ውይይትን የሚያጠናክር ትልቅ እሴት ተደርጎም ይወሰዳል። በአሁኑ ወቅት ቡና ለሀገሪቱ ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኝ ቀዳሚው የግብርና ምርት በመሆን ማዕከላዊ የኢኮኖሚ ሚናውን እየተጫወተ ይገኛል። አብዛኛው የኢትዮጵያ ቡና የሚመረተው በተፈጥሯዊ መንገድ በገበሬዎች ማሳ ላይ ወይም በዱር ውስጥ በመሆኑ፣ ለሰው ሰራሽ ማዳበሪያና ኬሚካል ተጋላጭ አይደለም። ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተመራጭነት ይበልጥ ከፍ አድርጎታል። ከኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ምሰሶ አንዱ የሆነው ቡናችን ለሀገሪቷ እያስገኘ ያለው ገቢም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ካነሷቸው ጉዳዮች መካከልም አንዱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዋልታ የሆነው ቡና ነበር። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከብራዚልና ኮሎምቢያ በመቀጠል በዓለም 3ኛዋ ትልቋ የቡና ላኪ ሀገር መሆኗን እና በአፍሪካም ቀዳሚ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጸዋል። በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ከቡና ወጪ ንግድ 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን፣ ይህ ውጤት ባለፉት 17 ዓመታት በድምሩ ከተገኘው 3 ነጥብ3 ቢሊዮን ዶላር ጋር ሲነጻጸር በዘርፉ የተመዘገበውን ከፍተኛ ዕድገት ያሳያል ብለዋል። ለተመዘገበው ውጤት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም አጠናክራ መጠቀም እንዳለባት ተናግረዋል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ የኢትዮጵያን የቡና ዘርፍ ከዘልማዳዊ አሰራር ወደ ዘመናዊ ምርታማነት ለማሸጋገር የሚያስችል አዲስ የ10 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ እና የተሻሻለ የልማት ፓኬጅ መዘጋጀቱን በቅርቡ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል። ቡና በሀገሪቱ ኢኮኖሚ፣ የሚሊዮን አርሶ አደሮች የኑሮ መሠረትና የወጪ ንግድ ዋነኛ ምሰሶ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ታላቅ ሀብት በጥራትና በዘላቂነት በማሳደግ ከምርት ወደ እሴት፣ ከእሴት ወደ ዓለም ገበያ ማሸጋገር የዘርፉ ዋነኛ አቅጣጫ መሆኑን ተናግረዋል። ይህንኑ ስትራቴጂ ለማሳካት የተጀመረው ሃገራዊ የቡና ምርትና ምርታማነት ኢኒሼቲቭ በአሁኑ ወቅት በሔክታር 9 ኩንታል የሆነውን የቡና ምርታማነት ወደ 21 ኩንታል ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ሚኒስትሩ አብራርተዋል። በተጨማሪም በ 1 ነጥብ15 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ላይ የቡና ልማት ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን፣ ለዚህም ምርጥ የቡና ዘር አጠቃቀም፣ የተቀናጀ የአፈር ንጥረ-ነገር፣ የቡና ተክል ጥግግት፣ የገረዛና የጥላ ዛፍ አያያዝ፣ የተቀናጀ የተባይ መከላከል፣ የመስኖ፣ የማዳበሪያ እንዲሁም የተሻሻለ የምርት አሰባሰብና የዕድሳት ሥራዎችን ያካተቱ ዘጠኝ የትኩረት መስኮች ተለይተው ወደ ሥራ መግባታቸውን አመልክተዋል። ይህ አዲሱ የቡና ልማት ኢኒሼቲቭ አርሶ አደሮችን፣ የማህበራትንና የባለሙያዎችን ግንዛቤና አቅም ለማሳደግ ሰፊ የንቅናቄ ሥራዎችን እንደሚከናውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በቡና ወጪ ንግድ ከአፍሪካ ቀዳሚና ከዓለም 3ኛዋ ትልቅ ላኪ ሀገር በመሆን ያሳየችው እመርታ፣ የዘርፉን ታላቅ የምጣኔ-ሀብት አቅም በተጨባጭ የሚያሳይ ነው። ለዚህ ደግሞ ላለፉት ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ምህዳር በማስተካከል ረገድ የራሱን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ይታወቃል። በዚህም መርሃ-ግብሩ በተጀመረበት 2011 ዓ.ም 600 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የተተከለው የቡና ችግኝ በየዓመቱ እያደገ በመሔድ በ2017 ዓ.ም ላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሸፈን ተችሏል። ይሄ በመሆኑም የቡና ምርታማነት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል። በ2011 ዓ.ም. ግማሽ ሚሊዮን ቶን የነበረው ዓመታዊ የቡና ምርት 2017 ዓም ላይ ወደ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ምርት ማግኘት በመቻሉ ኢኮኖሚው ላይ ያለውን ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ማስቀጠል ችሏል። በመሆኑም፣ የተያዘውን የተቀናጀ የልማት ስትራቴጂ በተግባር በመተርጎም የቡናን ምርት በጥራትና በብዛት ማሳደግ፣ የሀገሪቱን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት ከመደገፍ ባለፈ የኢትዮጵያን ቡና የወደፊት ጉዞ እና ዓለም አቀፋዊ መሪነት እጅግ አስተማማኝ ያደርገዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 11993
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 21747
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14780
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20525
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 104452
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79413
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57780
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55375
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 39659
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 39514
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 38991
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 37553
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 104452
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79413
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57780
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55375
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የአረቡ ዓለም ከግብፅ ምን አተረፈ?
Aug 19, 2026 78
የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ አካሄድ በታሪካዊ እውነታዎች እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ላይ እየተመሠረተ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ ጊዜ ያለፈባቸው የጂኦ ፖለቲካዊ የመጠላለፍ አካሄዶች ዋጋ ቢስነትና ጥቅም አልባነት በግልጽ እየታየ ይገኛል። ለብዙ አስርት ዓመታት ግብፅ የዓረብ ሊግን ለራሷ ጠባብ ፍላጎቶች እና ጂኦፖለቲካዊ አጀንዳዎች ማስፈጸሚያነት በሰፊው ስትጠቀምበት ቆይታለች። ሆኖም ይህ ጥቅምና ጉዳትን ብቻ መሰረት ያደረገ ግንኙነት አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ያስነሳል፦ ለመሆኑ የዓረቡ ዓለም ከግብፅ በምላሹ ያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? ለዚህ ጥያቄ አጭሩ መልስ ምንም የሚል ነው ሲል “What Has the Arab World Gained from Egypt? Why Ethiopia Belongs in the Arab League?” ፀሐፊው እና በፖለቲካና ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ በቋሚነት አስተያየት የሚሰጠው ጅብሪል ላሞ በኢዜአ እንግሊዘኛ ገጽ ባሳፈረው ሐተታ ላይ የግብጽ ፖሊሲዎች እንዲሁም ለሁለት አስርት ዓመታት የዘለቀው አምባገነናዊ አስተዳደር የጋራ ጥንካሬን ከመፍጠር ይልቅ የቀጣናውን አለመረጋጋት ማባባሳቸውን ገልጿል። እነዚህ ፖሊሲዎች፣ በምሥራቅ አፍሪካ እና በቀይ ባሕር አካባቢም ውጥረትን እያባባሱ እንደሚገኙ አመልክቷል። እነዚህ አካባቢዎች ለዓረቡ ዓለም የራቁ አይደሉም፤ ይልቁንም ለዓረቡ ዓለም ደኅንነት፣ የባሕር ንግድ፣ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የምግብ ዋስትና እጅግ ወሳኝ እና ስትራቴጂካዊ ማዕከላት ናቸው። የግብፅ ከፋፋይ ቀጣናዊ አካሄድ ከታዩባቸው ጉልህ ማሳያዎች አንዱ በኤርትራ ጉዳይ እና በሰፊው የኢትዮጵያ ግዛት አንድነት ላይ የነበራት ታሪካዊ ጣልቃ ገብነት ነው። ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ቀጣናዊ ተፅዕኖዋን ለመግታት በግብጽ ታስበው የተደራጁ ተገንጣይ ኃይሎችን እና ፖለቲካዊ ፕሮጀክቶችን በግልጽ እንደምትደግፍ ፀሐፊው አውስቷል። ከኢትዮጵያ የኤርትራ መገንጠል በምሥራቅ አፍሪካ ቀውስ የተሞላ ታሪክ ውስጥ አቢይ ክስተት ሲሆን፣ የውጭ ጂኦፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነቶች የሀገራትን እጣ ፈንታ እንዴት እንደሚያናጉ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የዲፕሎማሲ ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ የቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ እና የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ፣ ኢትዮጵያን ለማዳከም ታስቦ የተዘረጋውን የኤርትራን የመገንጠል ፕሮጀክት በመደገፍና በማፋጠን ረገድ ትልቅ ሚና ነበራቸው። በተጨማሪም ግብጽ በደቡባዊ የቀይ ባህር ቀጣና የምታካሂደው ቀውስ የመፍጠር እንቅስቃሴ፣ ለዓለም አቀፍ የባህር ንግድና ለቀጣናው ደህንነት ቀጥተኛ ስጋት ደቅኗል። በባብ-ኤል-ማንደብ የባሕር ወሽመጥ አካባቢ ውጥረቶችን በመቀስቀስ እና ተላላኪ ታጣቂ ቡድኖችን በማንቀሳቀስ፣ ወሳኝ የሆኑ የባህር መተላለፊያዎችን የጂኦፖለቲካዊ ግጭት መድረክ አድርጋዋለች። ይህም ለጠቅላላው የዓረብ ዓለም የኢነርጂና የምግብ አቅርቦት መሰረት የሆነውን የደህንነት መዋቅር አደጋ ላይ ጥሎታል፤ ሲሉ ጅብሪል ላሞ ያብራራሉ። ጅብሪል ላሞ በጽሑፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ የግብፅ ግልጽ የራስ ወዳድነት እንቅስቃሴዎች ቀጣናዊ ውጥረትን የሚፈጥሩ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ መቀላቀል ግን ለዓረቡ ዓለም እጅግ ከፍተኛ ጥቅም የሚያስገኝ ለውጥ አምጪ ዕድል ይዞ ይመጣል። በመደመር ፍልስፍና አሳታፊ ማዕቀፍ ሥር፣ ኢትዮጵያ ከማግለል ፖሊሲ ይልቅ የዓረቡን ዓለም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማስተሳሰር የሚያስችል የላቀ የዲፕሎማሲ አቅም አላት። በዚህም የአፍሪካ ዋነኛ የዲፕሎማሲ ማዕከል እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ የባለብዙ ወገን ትብብሮችን በመቅረጽ ረገድ ያላትን የካበተ ልምድ ታካፍላለች። የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ የመቀላቀል ጥረት ጊዜያዊ የፖለቲካ ስሌት ሳይሆን፣ የተፈጥሮ የታሪክ ጥሪ ነው። ከ135 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ፣ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እና ጥልቅ የሥልጣኔ መሠረት ያላት ይህች የቀይ ባሕር ሀገር፣ አባልነቷ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ መካከል ስትራቴጂካዊ ድልድይ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር ያላት ቁርኝት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በጋራ ታሪክ፣ ባህል እና የደም ትስስር ላይ የተገነባ ነው። እንደ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሉ የትምህርት ተቋማት፣ የኢትዮጵያ ጥናቶች በታሪክ ደረጃ ከመካከለኛው እና ከቅርብ ምሥራቅ ታሪክ (Near Eastern Studies) ተመድቦ መጠናቱ፤ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ከቀጣናው ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ ውህደት የሚያረጋግጥ ሕያው ማሳያ ነው። የባብ-ኤል-ማንደብ የባህር ወሽመጥ በጭራሽ መሰናክል አልነበረም፤ ይልቁንም ንግድን፣ ባህልን እና ማህበረሰቦችን በቀይ ባሕር በኩል ያገናኘ ዋንኛ መተላለፊያ ሆኖ አገልግሏል። ከንጉሥ አብረሃ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ በኢትዮጵያውያን እና በመካከለኛው ምሥራቅ ሕዝቦች መካከል የጋራ የደም ትስስር እንደነበር የሚያረጋግጡ ዘመናዊ የስነ ህይወት( ጄኔቲክስ) ጥናቶች፣ የዚህን ታሪካዊ ቁርኝት እውነተኛነት በግልጽ ያሳያሉ። በቋንቋና በባህል ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት መሠረት ታሪካዊ ትስስር ያለው ነው። የሀገሪቱ የቋንቋና የሥነ-ጽሑፍ ውርስ ከዓረብኛ፣ አራማይክና ዕብራይስጥ ጋር በጽኑ የተሳሰረ ሲሆን፣ ይህም በምሥራቅ አፍሪካና በአረቢያ ልሳነ-ምድር መካከል ያለውን ጥልቅ የጋራ የሥልጣኔ ቁርኝት ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ አላት። የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ተስደው በንጉስ ነጃሺ ከለላ ማግኘታቸው የእስልምናን ህልውና የታደገ ታሪካዊ ክስተት ሲሆን፣ ይህም ሀገሪቱን ከዓረቡ ዓለም ጋር በጽኑ አስተሳስሯታል። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ የዓረብ ሊግን በኢትዮጵያ ላይ እንደ ተቋማዊ ተፅዕኖ ማሳደሪያ መሣሪያ ግብጽ ስትጠቀምበት ቆይታለች። ግብፅ የውጭ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ዕድገት፣ የህዳሴውን ግድብም ሆነ የባሕር በር ጥያቄን እንደ ሥጋት በሚያይ ጊዜ ያለፈበት ስሌት ላይ የተመሠረተ ነው። ግብፅ የራሷን የውሃ አቋም በሊጉ ላይ በመጫን፣ ተቋሙ ከኢትዮጵያ ጋር አላስፈላጊ ውጥረት ውስጥ እንዲገባ አድርጋለች። ጅብሪል ላሞ እንዳመለከተው፣ ከግብጽ የአግላይነት ፖሊሲ ይልቅ የዘመኑ ነባራዊ ሁኔታዎች ሙሉ ትብብርን የሚጠይቁ ናቸው። በመደመር መርህ፣ ኢትዮጵያ ለዓረቡ ዓለም ለዘመናት ከቆዩ የጥላቻ መንገዶች በላቀ ሁኔታ የተሻሉ ጥቅሞችን ማቅረብ ትችላለች። እያደገ የመጣው የኢንዱስትሪ እና የአረንጓዴ ኃይል አቅሟ፣ ኢትዮጵያን ለቀይ ባህር ቀጣና የመረጋጋት ምሰሶ አድርጓታል። የመካከለኛው ምሥራቅ ቀጣና የውሃ እጥረት እና የምግብ ዋስትና ሥጋት በተጋረጠበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ የውሃ ሀበት እና ለም መሬት ለቀጣናው ወሳኝ የግብርና-ኢንዱስትሪ አጋር ያደርጋታል። የዓረብ ሊግ አባል ሀገራት የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ብሔረተኝነት በመሻገር፣ የቀይ ባህርን ቀጣና የሥልጣኔ እውነታ መቀበል ይኖርባቸዋል። አረብ ሊግ እንደ ጅቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ኮሞሮስ እና ሞሪታኒያ አባል ሀገራት መያዙ፣ ስብስቡ የተለያዩ ቀጣናዊ እውነታዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑን ያሳያሉ። የዓረብ ሊግ ሙሉ አባልነት የኢትዮጵያን አፍሪካዊ ማንነት ሳይቀንሰው፣ አህጉሩን ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር የሚያገናኝ ዋነኛ ድልድይ የሚያደርጋት በመሆኑ፤ ሊጉ የኢትዮጵያን አጋርነት በመቀበል ለአዲስ አበባ ተገቢውንና ሕጋዊ ቦታዋን የሚሰጥበት ጊዜ አሁን እንደሆነ በመግለጽ ጅብሪል ላሞ ፅሁፉን ቋጭቷል።
በምክክር እንጂ በመሳሪያ ድምጽ ሀገር አይገነባም
Aug 8, 2026 716
ኢትዮጵያ የዛሬ ማንነቷና ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እዚህ እንድትደርስ በርካታ ውጣውረዶችን አልፋለች። በቀደመ ታሪኳም ዜጎች በራሳቸው የውስጥ ጉዳይ መስማማት ባለመቻል እርስ በእርስ ካደረጓቸው ግጭቶች ባለፈ የውጭ ሃይሎችም የራሳቸውን አሉታዊ ጫና ሲፈጥሩ ቆይተዋል፤ አሁንም ይህንኑ ለማስቀጠል ተላላኪዎቻቸውን ለመጠቀም ሲሞክሩ ይታያል። በአንድ ሃገር ውስጥ የማያግባቡ ጉዳዮች በየትኛውም አጋጣሚና የታሪክ ምዕራፍ ሊያጋጥሙ ይችላሉ። እነዚህን ችግሮች በሃይል ለመፍታት የሚደረገው የመሳሪያ ትንቅንቅ ግን አክሳሪና ዘመን እያለፈበትም ነው። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ሰላማዊ የእድገት ጉዞ ለማወክ የህዝቦቿን አንድነት ለመበጥበጥ ከቅርብም ሆነ ከሩቅ የሚመጡ ጠላቶች ጠፍተው አያውቁም። በየዘመናቱ የተሻገርናቸው የታሪክ ስብራቶችን ፣ የመብት ጥያቄዎችንና ሌሎችንም መነሻ በማድረግ በውስጥ ባንዳዎች እና በውጭ ባዳዎች አማካኝነት የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ለመክተት፣ የብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚደረጉ ሴራዎች ዛሬም ላይ ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት ተሰሚነትና ተጽዕኖ የሚያሳምማቸው ለዜጎቿን እኩል ተጠቃሚነትና ብልጽግና መረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚያስጨንቃቸው እነዚህ ሃይሎች በመብት ፣ በነጻነት፣ በዴሞክራሲ፣ በማንነትና በሌሎችም የሃሰት ትርክቶች መነሻነት በሩቅ ቢያቅታቸው በቅርብ የውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን እያደራጁ በጀት መድበው የጦር መሳሪያ አቅርበው ሀገር የማፍረስ ሙከራቸውን አላቋረጡም። በመደመር እሳቤ ሁሉንም በአንድ ላይ በማቀራረብና የጋራ ትርክቶችን በመገንባት ከልዩነት ይልቅ የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ዘላቂ ልማቷን መፃኢ ብሩህ ተስፋዋን ለማለምለም በሁሉም ዘርፍ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ተሳትፎ እየሰራች መሆኗም ምቾት ነስቷቸዋል። በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሔደ ያለውና ወርቃማው እድል ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ፣ የሚያስችሉ ወሳኝ ምዕራፎች ላይ ደርሷል ። በዚህ የምክክር ሒደት በሀገሪቱ የትኛውም ጥግ ያለ ዜጋ እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የተወከሉበት ፣ የብሔር፣ የፖለቲካ አመለካከትና የሃይማኖት ልዩነት የማያደናቅፉት ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እየተካሔደ ይገኛል። ጥያቄያችንን በጠብመንጃ አፈሙዝ እንፈታለን ያሉ ታጣቂዎችም ብረት በማስቀመጥ አጀንዳዎቻቸውን ይዘው ወደ ጠረጴዛው ቀርበዋል። ልክ ናቸው ሀገር ከሁሉም ነገር ትበልጣለችና ይሄንን ወርቃማ እድል ለመጠቀም ማሰብ ትክክለኛው ውሳኔ ነው። በትጥቅ ትግል ጥያቄያችንን እንመልሳለን በሚል ሽፋን የሌሎችን አጀንዳ ለማሳካት የሚደረግ ጥረት የሃገርና የትውልድ ጠባሳ ከማስቀመጥና የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው መገንዘብ ብልህነት ነው። የዚህ ምክክር ተሳታፊ/ተመካካሪ ከሆኑት የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) አመራር ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በዚህ ይስማማሉ ። ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ተስፋ የጣልንበት፣ በንግግር፣ በምክክር ሀገራችንን የምናስቀጥልበት፣ ሁሉም ተነጋግሮ ተመካክሮ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ከችግሮች ነፃ የሚያደርግበት ነው ይላሉ። ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚነጋገርበት፣ የሚመካከርበት እና በሃሳብ የበላይነት ጠንካራ ሃገር የሚፈጠርበት መልካም የታሪክ አጋጣሚ መሆኑንም ይናገራሉ። በምክክር፣ በድርድር የሕዝብን ጥያቄ በመመለስ ሀገርን የምናስቀጥልበትና የውጭ ኃይሎችን ጣልቃ ገብነት የምናስወግድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ነው ብለዋል። የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራር የቀድሞ ታጣቂ ጃል ሰኚም ይሄንኑ ሃሳብ ይጋራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ለዓመታት የቆዩ ልዩነቶችን ለመፍታት ሀገራዊ ምክክር መዘጋጀቱ ትልቅ እርምጃ እንደመሆኑ እሳቸውም ያላቸውን ሀሳብ በማንጸባረቅ እየመከሩ ይገኛሉ። እርሳቸውና ቡድናቸው ከዚህ ቀደም የትጥቅ ትግልን በመምረጥ ጫካ ገብተው እንደነበር አስታውሰው፤ ችግሮችን በመሳሪያ ከመፍታት ይልቅ በሰላማዊ የምክክር መድረክ መፍታት ጥሩ አማራጭ መሆኑን አምነው ወደ ሰላም መንገድ መምጣታቸውንም ተናግረዋል። ችግሮቻቸውን በምክክር የፈቱ ሀገራት በሁሉም ዘርፍ ዕድገታቸውን የሚያስቀጥሉ ሲሆኑ ወደ ትጥቅ ትግል ያመሩና ግጭት ውስጥ የገቡት ደግሞ በፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውድቀት ለከፋ ድህነት መዳረጋቸውን ጠቅሰዋል። የጦር መሣሪያ በመነቅነቅና ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ በመግባት የሚፈታ ችግር እንደሌለ የሚናገሩት ደግሞ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ(አብን) አመራሩ ተመካካሪ ጣሒር መሀመድ ናቸው። ጫካ ባለውና እዚህ ባለው ሰው መካከል ምንም ዐይነት የዜግነት ልዩነት እንደሌለ ገልጸው ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሃሳብ ለመታገል ልዩነቱን ለማቅረብ የፈለገ ሁሉም ዜጋ በምክክሩ የመሳተፍ ነጻነት እንዳለው ገልጸዋል። በሃገራዊ ምክክሩ ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሰላማዊ መድረክ መወያየት የተመረጠበት ዋና ምክንያት ዘላቂ ሰላም፣ አገራዊ መግባባት እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ ለማምጣት ነው:: የትጥቅ ትግል የዜጎችን ህይወት ያጠፋል፣ መሰረተ ልማቶችን ያወድማል፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድቀትንም ያመጣል: ፤ ሰላማዊ መድረክ ግን ያለምንም ደም መፋሰስ ሃሳብን በሃሳብ ለመሞገት እድል ይሰጣል:: በኃይል የሚመጣ ለውጥ ብዙውን ጊዜ አሸናፊና ተሸናፊን ስለሚፈጥር የቁስል እና የቂም ዑደትን ያስቀጥላል:: በሰላማዊ ውይይት የሚገኝ መፍትሄ ግን የሁሉንም ወገን ስጋት እና ፍላጎት ያገናዘበ በመሆኑ ዘላቂነት ይኖረዋል:: ሃገራዊ ምክክሩ የታጠቁ አካላትም ጭምር መሳሪያቸውን አስቀምጠው በሃሳብ እንዲፎካከሩ መንገድ ከፍቷል። ይህ ታሪካዊና ወርቃማ እድል ኢትዮጵያዊንን አግባብቶ ወደተረጋጋችና የበለጸገች ሃገር የሚመራ በመሆኑ ስኬታማነቱ አያጠራጥርም። ለእድለኛው ትውልድ ያጋጠመው ወርቃማው ስጦታ ሃገራዊ ምክክር የተቋቋመለትን ዓላማ ያሳካል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም