ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በመደመር እሳቤ የህዳሴን ግድብ የመሰሉ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ለማሳካት ትብብራችንን ልናጠናክር ይገባል
Sep 17, 2025 34
ሚዛን አማን፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- በመደመር እሳቤ የህዳሴን ግድብ የመሰሉ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ለማሳካት በትብብር መንቀሳቀሱ ሊጠናከር እንደሚገባ ተመላከተ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሚዛን አማን ከተማ የታላቁን ሕዳሴ ግድብ መመረቅ ተከትሎ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄዷል። በሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ መሠረተ ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጅዮ ሳፒ እንዳሉት፤ በመደመር እሳቤ የህዳሴን ግድብ የመሰሉ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ለማሳካት ትብብራችንን ልናጠናክር ይገባል።   ለዚህም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የፈጠረውን መነቃቃት በሁሉም አካባቢ ሊጎለብትና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን ለማሳካት ሊውል ይገባል ብለዋል። ''የደምና የላብ ዋጋ የተከፈለበት የጋራ አሻራችን የሆነው ሕዳሴን መድገም ቀጣዩ ራእያችን ይሆናል'' ሲሉ ገልጸዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በበኩላቸው ወደ ሥልጣኔ ማማ ለመድረስ የተፈጥሮ ሀብታችንን አልምቶ መጠቀም መጀመራችን ትልቅ ትርጉም አለው ብለዋል።   የብልጽግና ጉዞ አመላካች የሆነው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከልማት ባሻገር የአገራዊ መግባባት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። አንድነታችን ፈተናን መሻገርያ ምርኩዛችን በመሆኑ የማይቻሉ የሚመስሉ ጉዳዮችን ችለን ለዓለም ማሳየታችንን መቀጠል አለብን ነው ያሉት። በይቻላል መንፈስ ግንባታው ተጠናቆ ወደ ኢኮኖሚ ምንጭነት የተቀየረው ዓባይ ታሪክ ከመናገር ታሪክ ወደ መሥራት እንድንሸጋገር አድርጎናል ያሉት ደግሞ የሚዛን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰሎሞን ሌዊ ናቸው።   በሰልፉ ላይ ከተገኙት የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ተስፋዬ ማሞ የግድቡ መመረቅ የመቻል ምልክት መሆኑን ተናግረዋል።   ሁሉም ኢትዮጵያውያን ላለፉት 14 ዓመታት ካላቸው ቀንሰው እያዋጡ አንድነታቸውን ያጸኑበት መሆኑን ገልጸው በቀጣይ መንግሥት የሚያስጀምራቸውን ፕሮጀክቶች በተሻለ መልኩ ለመደገፍ አነሳስቶናል ብለዋል።   ወይዘሮ ብርሃኔ ወርቁ በበኩላቸው በመተባበር የጀመርነው የሕዳሴ ግድብ መመረቁ፤ ጀምሮ ለመጨረስ አንድነት ትልቅ አቅም መሆኑን አረጋግጠዋል።
ብርሃኔ አደሬ - ኢትዮጵያን በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለበርካታ ጊዜ የወከለች አትሌት
Sep 17, 2025 41
ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1983 በፊንላንድ ሄልሲኒኪ ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አንስቶ በተካሄዱት ውድድሮች ላይ በሙሉ ተሳትፋለች። በነዚህ ሻምፒዮናዎች ላይ በርካታ አትሌቶች የኢትዮጵያ ስም እና ባንዲራ ከፍ ያደረጉ ገድሎችን ሰርተዋል። አትሌት ብርሃኔ አደሬ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሲነሳ ሁሌም አብራ እንድትነሳ የሚያደርግ ታሪክ አላት። በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያን በመወከልና ብዙ ጊዜ በመሳተፍ የአጠቃላይ ቀዳሚነቱን ደረጃ የያዘችው ብርሃኔ አደሬ ናት። ብርሃኔ ከእ.አ.አ 1993 እስከ 2005 በተካሄዱ ሰባት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናዎች ላይ ተሳትፋለች። አትሌቷ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው እ.አ.አ በ1993 በጀርመን ስቱትጋርት በተካሄደው አራተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ነበር። በ10000 ሜትር ሴቶች ውድድር ማጣሪያ ተሳትፋ ለፍጻሜው ማለፍ አልቻለችም። በስዊድን ጉተንበርግ እ.አ.አ በ1995 በተካሄደው አምስተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ10000 ሜትር ሴቶች ብትወዳደርም ማጣሪያውን አላለፈችም። ብርሃኔ እ.አ.አ በ1997 በግሪክ አቴንስ በተካሄደው ስድስተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ10000 ሜትር ፍጻሜ ተወዳድራ አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። 31 ደቂቃ ከ49 ሴኮንድ ከ17 ማይክሮ ሴኮንድ ውድድሩን ለማጠናቀቅ የፈጀባት ጊዜ ነበር። በስፔን ሲቪያ እ.አ.አ በ1999 በተካሄደው ሰባተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በድጋሚ በ10000 ሜትር ፍጻሜ ተወዳድራ 31 ደቂቃ ከ29 ሴኮንድ ከ11 ማይክሮ ሴኮንድ ሰባተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። አትሌት ብርሃኔ የመጀመሪያ ሜዳሊያዋን ያገኘችው እ.አ.አ በ2001 በካናዳ ኤድመንተን በተደረገው ስምንተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ነው። አትሌቷ በ10000 ሜትር ፍጻሜ 31 ደቂቃ ከ48 ሴኮንድ ከ85 ማይክሮ ሴኮንድ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። በውድድሩ የወርቅ ሜዳሊያውን ያገኘችው አትሌት ደራርቱ ቱሉ ነበረች። እ.አ.አ በ2003 በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው ዘጠነኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለብርሃኔ ትልቁን ስኬት ያገኝችበት ሆኖ አልፏል። አትሌት ብርሃኔ በ10000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ 30 ደቂቃ ከ04 ሴኮንድ ከ18 ማይክሮ ሴኮንድ የወርቅ ሜዳሊያ አገኝታለች። በርቀቱ የሻምፒዮናውን ክብረ ወሰን አሻሽላለች። በወቅቱ በ5000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ ተሳትፋ 10ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ብርሃኔ የመጨረሻ የሻምፒዮና ተሳትፏዋን ያደረገችው እ.አ.አ በ2005 በፊንላንድ ሄልሲንኪ በተካሄደው 10ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ነበር። በ10000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን ተከትላ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አገኝታለች። 30 ደቂቃ ከ25 ሴኮንድ ከ41 ማይክሮ ሴኮንድ ውድድሩን ለማጠናቀቅ የፈጀባት ጊዜ ነበር። አትሌት ብርሃኔ አደሬ በሻምፒዮናው ተሳትፎ አንድ የወርቅ እና ሁለት የብር ሜዳሊያዎችን አግኝታለች። አትሌቷ በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና እና በአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮናዎች ላይም ኢትዮጵያን ወክላ ተወዳድራለች። ብርሃኔ ራሷን ከውድድር ከማግለሏ በፊት በግማሽ ማራቶን እና ማራቶን ውድድሮች ላይ ተሳትፎ አድርጋለች። አትሌት ብርሃኔ አደሬ እና የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሁሌም ሲወሳ የሚኖሩ የታሪክ ትስስሮሽ አላቸው።
የመደመር መንግሥት ማደግ ለሚፈልጉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ ነው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 38
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የመደመር መንግሥት መጽሐፍ፤ ጊዜ ተሰጥቶናል በግልጽ ምልከታና እሳቤ ሀገራችንን ብንሠራ ታሪክ ሠሪዎች እንጂ ዘካሪዎች አንሆንም በሚል የተዘጋጀ ሠነድ ነው ብለዋል። ይህም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት ማጠንጠኛው “አራት መ” መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የመጀመሪያው “መ” መነሻ ነው ብለዋል። መነሻውም ቁጭት መሆኑን ነው ያስረዱት። ኢትዮጵያ ለምን ድሃ ሆነች? ኢትዮጵያ ለምን ተረጂ ሆነች? ኢትዮጵያ ከማን ስለምታንስ ነው ከማን የምትረዳው? የሚሉ የቁጭት ጥያቄዎች እና ምክንያት ፍለጋ ነው መነሻው ብለዋል። አሳማኝ ምክንያት ካልተገኘለት ቁጭት ያንገበግባል፤ እንቅልፍ ይነሳል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ለመደመር መንግሥት መነሻ ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ምንም እንኳን በርካታ ድሃ ሀገራት ቢኖሩም የኢትዮጵያ ድሃ መሆን የሚያንገበግበው ግን፤ ምድረ ቀደምት መሆኗ፣ የነጻነት ገድል ያላት፣ በባህልና በታሪክ የሚያኮራ ሥራ ያላት በመሆኗ ነው ብለዋል። እንደ ምድረ ቀደምትነት የግብርና ሥራን ቀድመን ብንጀምርም፤ እስካሁን አሠራራችን በሚፈለገው ልክ በቴክኖሎጂ አለማደጉ ይቆጫል። በሽመና እንዲሁም በባህል መድኃኒት ነባር ልምድ ያለን ሀገር እንዴት በስፋት ማምረት እና ራሳችንን መቻል ተሳነን? የሚል ቁጭት መነሻ መሆኑንም አስረድተዋል። ከቁጭት በተጨማሪ መንፈሳዊ ቅናት ለመደመር መንግሥት መነሻ እንደሆነም አብራርተዋል። የመደመር መንግሥት ከተገነዘባቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል፤ የተዛቡ ጥያቄዎች መኖር እና ለዚህም ደግሞ አፍራሽ የለውጥ ሂደት መከተል የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል። የሕዳሴ ግድብ አንድ መንግሥትና ግለሰብ ስኬት ሳይሆን፤ የመላ ኢትዮጵያውን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ገድል መሆኑንም አስረድተዋል።
የእኛ መሻት የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 48
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የእኛ መሻት የምትመስል ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ የመደመር መንግሥት ውጤት ከሰማነው፣ ካነበብነው ብቻ ሳይሆን በተግባር ስንሞክር ካየነው ውጣ ውረድ ጭምር የተቀዳ ነው ብለዋል። በዚህም ብዙዎች የሚማሩበት፣ የሚያሳድጉት፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የሚተጉበት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም ነው ያሉት። የመፈጸም ብቃታችንን በብዙ መንገድ ዐይተናል፤ የእኛ መሻት የምትመስል ሀገር ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። ብዙ ጊዜ ለመምሰል ሞክረን አልተሳካም፤ አሁን በእኛ መልክ፣ በእኛ እሳቤ፣ በእኛ ባህል ልክ ተቀርጾ በምሳሌነት የሚወሰድ ሀገር መገንባት እንፈልጋለን ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እንደሚቻልም የመደመር መንግሥት በጽኑ ያምናል ሲሉ አስረድተዋል። ለአብነትም የአረንጓዴ ዐሻራን ሥራ ጠቅሰው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ 48 ቢሊየን ችግኝ መትከል በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ማንም ያልሞከረው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የምንመሰልበት ሆኖ በታሪክ ማኅደር ይቀመጣል ነው ያሉት በንግግራቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም በትጋትና በቅንጅት ያሰብነውን ማሳካት እንደምንችል ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።
የሚታይ
የመደመር መንግሥት ማደግ ለሚፈልጉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ ነው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 38
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የመደመር መንግሥት መጽሐፍ፤ ጊዜ ተሰጥቶናል በግልጽ ምልከታና እሳቤ ሀገራችንን ብንሠራ ታሪክ ሠሪዎች እንጂ ዘካሪዎች አንሆንም በሚል የተዘጋጀ ሠነድ ነው ብለዋል። ይህም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት ማጠንጠኛው “አራት መ” መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የመጀመሪያው “መ” መነሻ ነው ብለዋል። መነሻውም ቁጭት መሆኑን ነው ያስረዱት። ኢትዮጵያ ለምን ድሃ ሆነች? ኢትዮጵያ ለምን ተረጂ ሆነች? ኢትዮጵያ ከማን ስለምታንስ ነው ከማን የምትረዳው? የሚሉ የቁጭት ጥያቄዎች እና ምክንያት ፍለጋ ነው መነሻው ብለዋል። አሳማኝ ምክንያት ካልተገኘለት ቁጭት ያንገበግባል፤ እንቅልፍ ይነሳል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ለመደመር መንግሥት መነሻ ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ምንም እንኳን በርካታ ድሃ ሀገራት ቢኖሩም የኢትዮጵያ ድሃ መሆን የሚያንገበግበው ግን፤ ምድረ ቀደምት መሆኗ፣ የነጻነት ገድል ያላት፣ በባህልና በታሪክ የሚያኮራ ሥራ ያላት በመሆኗ ነው ብለዋል። እንደ ምድረ ቀደምትነት የግብርና ሥራን ቀድመን ብንጀምርም፤ እስካሁን አሠራራችን በሚፈለገው ልክ በቴክኖሎጂ አለማደጉ ይቆጫል። በሽመና እንዲሁም በባህል መድኃኒት ነባር ልምድ ያለን ሀገር እንዴት በስፋት ማምረት እና ራሳችንን መቻል ተሳነን? የሚል ቁጭት መነሻ መሆኑንም አስረድተዋል። ከቁጭት በተጨማሪ መንፈሳዊ ቅናት ለመደመር መንግሥት መነሻ እንደሆነም አብራርተዋል። የመደመር መንግሥት ከተገነዘባቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል፤ የተዛቡ ጥያቄዎች መኖር እና ለዚህም ደግሞ አፍራሽ የለውጥ ሂደት መከተል የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል። የሕዳሴ ግድብ አንድ መንግሥትና ግለሰብ ስኬት ሳይሆን፤ የመላ ኢትዮጵያውን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ገድል መሆኑንም አስረድተዋል።
የእኛ መሻት የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 48
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የእኛ መሻት የምትመስል ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ የመደመር መንግሥት ውጤት ከሰማነው፣ ካነበብነው ብቻ ሳይሆን በተግባር ስንሞክር ካየነው ውጣ ውረድ ጭምር የተቀዳ ነው ብለዋል። በዚህም ብዙዎች የሚማሩበት፣ የሚያሳድጉት፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የሚተጉበት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም ነው ያሉት። የመፈጸም ብቃታችንን በብዙ መንገድ ዐይተናል፤ የእኛ መሻት የምትመስል ሀገር ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። ብዙ ጊዜ ለመምሰል ሞክረን አልተሳካም፤ አሁን በእኛ መልክ፣ በእኛ እሳቤ፣ በእኛ ባህል ልክ ተቀርጾ በምሳሌነት የሚወሰድ ሀገር መገንባት እንፈልጋለን ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እንደሚቻልም የመደመር መንግሥት በጽኑ ያምናል ሲሉ አስረድተዋል። ለአብነትም የአረንጓዴ ዐሻራን ሥራ ጠቅሰው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ 48 ቢሊየን ችግኝ መትከል በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ማንም ያልሞከረው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የምንመሰልበት ሆኖ በታሪክ ማኅደር ይቀመጣል ነው ያሉት በንግግራቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም በትጋትና በቅንጅት ያሰብነውን ማሳካት እንደምንችል ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።
የምንደመረው ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 110
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች ብለዋል። ለሀገራዊ ዕድገታችን ሁነኛው መንገድ መተባበር እና መደመር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።   ኢትዮጵያ በምሳሌነት እንድትጠቀስ የሚያስችሉ በርካታ ራዕዮቻችንን ለማሳካት መነሻ ከያዝን፣ መዳረሻ ከአበጀን በኋላ እንዴት ባለ መንገድ መፈጸም አለብን የሚለው ትልቅ ጉዳይ መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህ ደግሞ በእንዴት ያለ መንገድ እንሂድ የሚለው በመደመር መንግሥት መመላከቱን አንስተዋል። በዚህም መሠረት ራዕዮቻችንን ለማሳካት ከሚረዱ መንገዶች መካከል አንዱ ከውስጥ ወደ ውጭ መመልከት ነው ብለዋል። በየዘርፉ የካበተ ዕውቀት ያላት ኢትዮጵያ ለማስተማር እንጂ ከሌሎች ለመማር የምትጓጓ መሆን እንደሌለባትም ጠቅሰዋል። ያለፉን፣ የቀደሙን፣ የሰለጠኑ፣ የፈጠሩ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህ የሚበጀንን መቅዳት ሳይሆን መማር ይጠቅማል ብለዋል። ከሌሎች ሀገራት ስንማርም የእኛን መርምረንና አሰናስለን ግልጽ ሐሳብ መያዝ ስንችል፤ የአቅምና አቋም ድምር ስንፈጥር መሆን አለበት ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ውስጥ የአቅም እና አቋም ድምር ከፈጠርን ተዓምር መሥራት እንችላለን ሲሉም ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር)
Sep 17, 2025 97
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።   በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግርም፤ የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያውያንን በጋራ ራዕይ ላይ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ብለዋል። ኢትዮጵያውያን በጋራ ራዕይ ላይ ከተሰባሰቡ በኋላ፤ ስብራት ለይተን መፍትሔ ማበጀት ያስፈልጋል ሲሉም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የእድገት ጉዞ እና የፖለቲካ ችግር ስብራት የጠላቶቻችን አጀንዳ የሆነው መለያየት ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህ መፈወሻ መድኃኒቱ ደግሞ መደመር ብቻ ነው ሲሉ አስረድተዋል። በጋራ መቆም ብንችል መፍጠን እንችላለን፤ መፍጠር እንችላለን፤ በአስፈላጊው ቦታ ደግሞ መከተል ሳይሆን መዝለል እንችላለን ነው ያሉት።   አክለውም በጋራ ስንቆም ከተቀባይነትና ተከታይነት መላቀቅ እንችላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሐሳብ ተቀብለን፣ ገንዘብ ተቀብለን፣ ተልዕኮ ተቀብለን ኢትዮጵያ ላይ መለማመድ ተገቢ አይደለም በማለት በአጽንኦት ገልጸዋል። በሥነ-ልቦና ስብራት መኖሩንና ጥሩ ነገሮች ሲታዩ የኢትዮጵያ እንደሆነ ያለመቀበል ተገቢነት የሌለው ልምምድ መኖሩንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እንደምትችል እና በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኗን መቀበል እንደሚገባም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መክረዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የመደመር መንግሥት ማደግ ለሚፈልጉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ ነው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 38
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የመደመር መንግሥት መጽሐፍ፤ ጊዜ ተሰጥቶናል በግልጽ ምልከታና እሳቤ ሀገራችንን ብንሠራ ታሪክ ሠሪዎች እንጂ ዘካሪዎች አንሆንም በሚል የተዘጋጀ ሠነድ ነው ብለዋል። ይህም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት ማጠንጠኛው “አራት መ” መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የመጀመሪያው “መ” መነሻ ነው ብለዋል። መነሻውም ቁጭት መሆኑን ነው ያስረዱት። ኢትዮጵያ ለምን ድሃ ሆነች? ኢትዮጵያ ለምን ተረጂ ሆነች? ኢትዮጵያ ከማን ስለምታንስ ነው ከማን የምትረዳው? የሚሉ የቁጭት ጥያቄዎች እና ምክንያት ፍለጋ ነው መነሻው ብለዋል። አሳማኝ ምክንያት ካልተገኘለት ቁጭት ያንገበግባል፤ እንቅልፍ ይነሳል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ለመደመር መንግሥት መነሻ ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ምንም እንኳን በርካታ ድሃ ሀገራት ቢኖሩም የኢትዮጵያ ድሃ መሆን የሚያንገበግበው ግን፤ ምድረ ቀደምት መሆኗ፣ የነጻነት ገድል ያላት፣ በባህልና በታሪክ የሚያኮራ ሥራ ያላት በመሆኗ ነው ብለዋል። እንደ ምድረ ቀደምትነት የግብርና ሥራን ቀድመን ብንጀምርም፤ እስካሁን አሠራራችን በሚፈለገው ልክ በቴክኖሎጂ አለማደጉ ይቆጫል። በሽመና እንዲሁም በባህል መድኃኒት ነባር ልምድ ያለን ሀገር እንዴት በስፋት ማምረት እና ራሳችንን መቻል ተሳነን? የሚል ቁጭት መነሻ መሆኑንም አስረድተዋል። ከቁጭት በተጨማሪ መንፈሳዊ ቅናት ለመደመር መንግሥት መነሻ እንደሆነም አብራርተዋል። የመደመር መንግሥት ከተገነዘባቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል፤ የተዛቡ ጥያቄዎች መኖር እና ለዚህም ደግሞ አፍራሽ የለውጥ ሂደት መከተል የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል። የሕዳሴ ግድብ አንድ መንግሥትና ግለሰብ ስኬት ሳይሆን፤ የመላ ኢትዮጵያውን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ገድል መሆኑንም አስረድተዋል።
የእኛ መሻት የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 48
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የእኛ መሻት የምትመስል ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ የመደመር መንግሥት ውጤት ከሰማነው፣ ካነበብነው ብቻ ሳይሆን በተግባር ስንሞክር ካየነው ውጣ ውረድ ጭምር የተቀዳ ነው ብለዋል። በዚህም ብዙዎች የሚማሩበት፣ የሚያሳድጉት፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የሚተጉበት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም ነው ያሉት። የመፈጸም ብቃታችንን በብዙ መንገድ ዐይተናል፤ የእኛ መሻት የምትመስል ሀገር ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። ብዙ ጊዜ ለመምሰል ሞክረን አልተሳካም፤ አሁን በእኛ መልክ፣ በእኛ እሳቤ፣ በእኛ ባህል ልክ ተቀርጾ በምሳሌነት የሚወሰድ ሀገር መገንባት እንፈልጋለን ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እንደሚቻልም የመደመር መንግሥት በጽኑ ያምናል ሲሉ አስረድተዋል። ለአብነትም የአረንጓዴ ዐሻራን ሥራ ጠቅሰው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ 48 ቢሊየን ችግኝ መትከል በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ማንም ያልሞከረው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የምንመሰልበት ሆኖ በታሪክ ማኅደር ይቀመጣል ነው ያሉት በንግግራቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም በትጋትና በቅንጅት ያሰብነውን ማሳካት እንደምንችል ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።
የምንደመረው ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 110
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች ብለዋል። ለሀገራዊ ዕድገታችን ሁነኛው መንገድ መተባበር እና መደመር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።   ኢትዮጵያ በምሳሌነት እንድትጠቀስ የሚያስችሉ በርካታ ራዕዮቻችንን ለማሳካት መነሻ ከያዝን፣ መዳረሻ ከአበጀን በኋላ እንዴት ባለ መንገድ መፈጸም አለብን የሚለው ትልቅ ጉዳይ መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህ ደግሞ በእንዴት ያለ መንገድ እንሂድ የሚለው በመደመር መንግሥት መመላከቱን አንስተዋል። በዚህም መሠረት ራዕዮቻችንን ለማሳካት ከሚረዱ መንገዶች መካከል አንዱ ከውስጥ ወደ ውጭ መመልከት ነው ብለዋል። በየዘርፉ የካበተ ዕውቀት ያላት ኢትዮጵያ ለማስተማር እንጂ ከሌሎች ለመማር የምትጓጓ መሆን እንደሌለባትም ጠቅሰዋል። ያለፉን፣ የቀደሙን፣ የሰለጠኑ፣ የፈጠሩ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህ የሚበጀንን መቅዳት ሳይሆን መማር ይጠቅማል ብለዋል። ከሌሎች ሀገራት ስንማርም የእኛን መርምረንና አሰናስለን ግልጽ ሐሳብ መያዝ ስንችል፤ የአቅምና አቋም ድምር ስንፈጥር መሆን አለበት ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ውስጥ የአቅም እና አቋም ድምር ከፈጠርን ተዓምር መሥራት እንችላለን ሲሉም ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር)
Sep 17, 2025 97
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።   በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግርም፤ የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያውያንን በጋራ ራዕይ ላይ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ብለዋል። ኢትዮጵያውያን በጋራ ራዕይ ላይ ከተሰባሰቡ በኋላ፤ ስብራት ለይተን መፍትሔ ማበጀት ያስፈልጋል ሲሉም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የእድገት ጉዞ እና የፖለቲካ ችግር ስብራት የጠላቶቻችን አጀንዳ የሆነው መለያየት ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህ መፈወሻ መድኃኒቱ ደግሞ መደመር ብቻ ነው ሲሉ አስረድተዋል። በጋራ መቆም ብንችል መፍጠን እንችላለን፤ መፍጠር እንችላለን፤ በአስፈላጊው ቦታ ደግሞ መከተል ሳይሆን መዝለል እንችላለን ነው ያሉት።   አክለውም በጋራ ስንቆም ከተቀባይነትና ተከታይነት መላቀቅ እንችላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሐሳብ ተቀብለን፣ ገንዘብ ተቀብለን፣ ተልዕኮ ተቀብለን ኢትዮጵያ ላይ መለማመድ ተገቢ አይደለም በማለት በአጽንኦት ገልጸዋል። በሥነ-ልቦና ስብራት መኖሩንና ጥሩ ነገሮች ሲታዩ የኢትዮጵያ እንደሆነ ያለመቀበል ተገቢነት የሌለው ልምምድ መኖሩንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እንደምትችል እና በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኗን መቀበል እንደሚገባም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መክረዋል።
የመደመር መንግሥት ከትናንት እስረኝነት የተላቀቀና ለምክንያታዊነት ትኩረት የሰጠ ነው
Sep 17, 2025 109
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት ከትናንት እስረኝነት የተላቀቀና ለምክንያታዊነት ትኩረት የሰጠ መሆኑን በመደመር መንግሥት መጽሃፍ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀረቡ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በመደመር እሳቤ የጻፉት 4ኛው መጽሃፍ ''የመደመር መንግሥት'' ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። በመጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመጽሃፉ ደራሲና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል። በመጽሃፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር ዳኛቸው አሰፋ(ዶ/ር)፣ መጽሃፉ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ችግሮች ላይ ንደፈ ሃሳባዊ ትንተና ብቻ ሳይሆን ተግባራዊ ምላሽ የሚያመላክት መሆኑንም አብራርተዋል።   ለችግሮች አውዱን የተገነዘበ ሙሉ መፍትሄ ማስቀመጥ እንደሚገባ በመጽሃፉ በግልጽ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ይህም አንድ መንገድን ብቻ ከሚከተል የርዕዮት እስረኝነት የተላቀቀ አካሄድ ነው ብለዋል። መጽሃፉ የያዛቸው ትንተናዎች በምክንያታዊነት ላይ ያረፉና ለምክንያታዊነት ክፍት መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል። መጽሃፉ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የት እንዳለችና መጻኢ ጉዞዋ ምን መምሰል እንዳለበትም በግልጽ ያስቀምጣል ነው ያሉት። በተጨማሪም በዜጎች መካከል መተባበርና መደጋገፍ እንዲኖር መንገድ በማሳየት ሰላምና አብሮነት እንዲጎለብት ዝርዝር ሃሳብ ማስቅመጡንም አንስተዋል።   ሌላኛው በመጽሃፉ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀረቡት የፖለቲካ ተንታኙ ዘሪሁን ተሾመ በበኩላቸው፤ መጽሃፉ ትናትን በልኩ የሚገነዘብና በትናንት እሳቤ ላይ ያልቆመ ስለመሆኑ አብራርተዋል። የዛሬ ችግሮችን በተገቢው መንገድ እንደሚዳስስ ጠቅሰው፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች የተሻለ ነገን ከመገንባት የሚያስቆሙ እንዳልሆኑ በግልጽ እንደሚያመላክትም ነው ያነሱት። በመጽሃፉ የተዳሰሱ ሃሳቦችም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ የሚበጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
የመደመር መንግስት መጽሃፍ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰና መፍትሄ ያመላከተ ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Sep 17, 2025 139
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግስት መጽሃፍ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰና መፍትሄ ያመላከተ ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጻፈው የመደመር መንግስት መጽሃፍ ዛሬ ለንባብ በቅቷል። በመጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ፕሬዝዳነት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመጽሃፉ ደራሲና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል። በመጽሐፍ ላይ ዳሰሳ ካቀረቡት መካከል የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ እንዳሉት፣ መጽሃፉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሁኔታ የሚያስቃኝ ነው።   በተለይ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰ እና ተግባራዊ መፍትሄዎችን ያመላከተ መሆኑንም ተናግረዋል። መጽሃፍ አስተሳሰብ ላይ ትኩረት አድርጎ ከቁጭት እንደሚነሳ ጠቅሰው፣ ይህም ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ነው ያብራሩት። መጽሃፉ ነገሮችን አፍርሶ ከመስራት ይልቅ አዎንታዊውን ማስቀጠል፣ አሉታዊውን ደግሞ ማስተካከልን እንደሚያመላክትም አንስተዋል። ይህም ኢትዮጵያ ለዘመናት የሄደችበትን ተቸካይ የፖለቲካ አካሄድ የቀየረ አተያይ ስለመሆኑም አብራርተዋል። መጽሃፉ ፖለቲካችን ያሸነፈ አካል እንደፈለገ ሁሉን ይጠቅልል ከሚል አካሄድ የሚያወጣ ነው ብለዋል። ''እኔ የፈለኩት ካልሆነ'' ከሚል የዜሮ ድምር ጨዋታ መውጣት የሚቻልበትን ዘመናዊ የፖለቲካ አካሄድ ያመላከተ ስለመሆኑም አቶ ጌታቸው አብራርተዋል። በሌላ በኩል ዜጎች ከመሰረታዊ ፍላጎት ባሻገር በክብር የመኖር ህልማቸውን ለመመለስ አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ችግሮች በነበረው አካሄድ ትርጉም ባለው መልኩ መፍታት እንደማይቻል አንስተው፣ የመደመር እሳቤ ተግባራዊ ያደረገው መፍጠርና መፍጠን በዚህ ረገድ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማን የተከማቸ ችግር ለመፍታት የተተገበረው የመፍጠርና መፍጠን መፍትሄ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ መሆኑንም ተናግረዋል። አዲስ አበባን ለመለወጥ የተጀመረው ስራ አዲስ የስራ ባህልን ያለማመደ መሆኑንም ገልጸዋል። በቀጣይ በአዲስ አበባ የታየው አዲስ ተስፋ ወደ ሁሉም የኢትዮጵያ አቅጣጫ እንዲሰፋ መረባረብ ይገባል ነው ያሉት። መጽሃፉ ለማንበብ ምቹ በሆነ አቀራረብ መዘጋጀቱን የተናገሩት አቶ ጌታቸው፣ ሁሉም እንዲያነበውም ጥሪ አቅርበዋል።
ፖለቲካ
የመደመር መንግሥት ማደግ ለሚፈልጉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ ነው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 38
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የመደመር መንግሥት መጽሐፍ፤ ጊዜ ተሰጥቶናል በግልጽ ምልከታና እሳቤ ሀገራችንን ብንሠራ ታሪክ ሠሪዎች እንጂ ዘካሪዎች አንሆንም በሚል የተዘጋጀ ሠነድ ነው ብለዋል። ይህም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ማደግና መለወጥ ለሚፈልጉ ሀገራት በሙሉ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት ማጠንጠኛው “አራት መ” መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የመጀመሪያው “መ” መነሻ ነው ብለዋል። መነሻውም ቁጭት መሆኑን ነው ያስረዱት። ኢትዮጵያ ለምን ድሃ ሆነች? ኢትዮጵያ ለምን ተረጂ ሆነች? ኢትዮጵያ ከማን ስለምታንስ ነው ከማን የምትረዳው? የሚሉ የቁጭት ጥያቄዎች እና ምክንያት ፍለጋ ነው መነሻው ብለዋል። አሳማኝ ምክንያት ካልተገኘለት ቁጭት ያንገበግባል፤ እንቅልፍ ይነሳል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ለመደመር መንግሥት መነሻ ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ምንም እንኳን በርካታ ድሃ ሀገራት ቢኖሩም የኢትዮጵያ ድሃ መሆን የሚያንገበግበው ግን፤ ምድረ ቀደምት መሆኗ፣ የነጻነት ገድል ያላት፣ በባህልና በታሪክ የሚያኮራ ሥራ ያላት በመሆኗ ነው ብለዋል። እንደ ምድረ ቀደምትነት የግብርና ሥራን ቀድመን ብንጀምርም፤ እስካሁን አሠራራችን በሚፈለገው ልክ በቴክኖሎጂ አለማደጉ ይቆጫል። በሽመና እንዲሁም በባህል መድኃኒት ነባር ልምድ ያለን ሀገር እንዴት በስፋት ማምረት እና ራሳችንን መቻል ተሳነን? የሚል ቁጭት መነሻ መሆኑንም አስረድተዋል። ከቁጭት በተጨማሪ መንፈሳዊ ቅናት ለመደመር መንግሥት መነሻ እንደሆነም አብራርተዋል። የመደመር መንግሥት ከተገነዘባቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል፤ የተዛቡ ጥያቄዎች መኖር እና ለዚህም ደግሞ አፍራሽ የለውጥ ሂደት መከተል የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል። የሕዳሴ ግድብ አንድ መንግሥትና ግለሰብ ስኬት ሳይሆን፤ የመላ ኢትዮጵያውን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ገድል መሆኑንም አስረድተዋል።
የእኛ መሻት የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 48
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- የእኛ መሻት የምትመስል ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ ተመርቋል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ የመደመር መንግሥት ውጤት ከሰማነው፣ ካነበብነው ብቻ ሳይሆን በተግባር ስንሞክር ካየነው ውጣ ውረድ ጭምር የተቀዳ ነው ብለዋል። በዚህም ብዙዎች የሚማሩበት፣ የሚያሳድጉት፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የሚተጉበት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም ነው ያሉት። የመፈጸም ብቃታችንን በብዙ መንገድ ዐይተናል፤ የእኛ መሻት የምትመስል ሀገር ሳይሆን የምትመሰል ሀገር መፍጠር ነው ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። ብዙ ጊዜ ለመምሰል ሞክረን አልተሳካም፤ አሁን በእኛ መልክ፣ በእኛ እሳቤ፣ በእኛ ባህል ልክ ተቀርጾ በምሳሌነት የሚወሰድ ሀገር መገንባት እንፈልጋለን ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እንደሚቻልም የመደመር መንግሥት በጽኑ ያምናል ሲሉ አስረድተዋል። ለአብነትም የአረንጓዴ ዐሻራን ሥራ ጠቅሰው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ 48 ቢሊየን ችግኝ መትከል በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ማንም ያልሞከረው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የምንመሰልበት ሆኖ በታሪክ ማኅደር ይቀመጣል ነው ያሉት በንግግራቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም በትጋትና በቅንጅት ያሰብነውን ማሳካት እንደምንችል ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።
የምንደመረው ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 17, 2025 110
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች ብለዋል። ለሀገራዊ ዕድገታችን ሁነኛው መንገድ መተባበር እና መደመር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ስለ አንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።   ኢትዮጵያ በምሳሌነት እንድትጠቀስ የሚያስችሉ በርካታ ራዕዮቻችንን ለማሳካት መነሻ ከያዝን፣ መዳረሻ ከአበጀን በኋላ እንዴት ባለ መንገድ መፈጸም አለብን የሚለው ትልቅ ጉዳይ መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህ ደግሞ በእንዴት ያለ መንገድ እንሂድ የሚለው በመደመር መንግሥት መመላከቱን አንስተዋል። በዚህም መሠረት ራዕዮቻችንን ለማሳካት ከሚረዱ መንገዶች መካከል አንዱ ከውስጥ ወደ ውጭ መመልከት ነው ብለዋል። በየዘርፉ የካበተ ዕውቀት ያላት ኢትዮጵያ ለማስተማር እንጂ ከሌሎች ለመማር የምትጓጓ መሆን እንደሌለባትም ጠቅሰዋል። ያለፉን፣ የቀደሙን፣ የሰለጠኑ፣ የፈጠሩ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህ የሚበጀንን መቅዳት ሳይሆን መማር ይጠቅማል ብለዋል። ከሌሎች ሀገራት ስንማርም የእኛን መርምረንና አሰናስለን ግልጽ ሐሳብ መያዝ ስንችል፤ የአቅምና አቋም ድምር ስንፈጥር መሆን አለበት ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ውስጥ የአቅም እና አቋም ድምር ከፈጠርን ተዓምር መሥራት እንችላለን ሲሉም ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር)
Sep 17, 2025 97
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት በጋራ ራዕይ ላይ መሰባሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተፃፈው "የመደመር መንግሥት" መፅሐፍ ትናንት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።   በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግርም፤ የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያውያንን በጋራ ራዕይ ላይ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ያምናል ብለዋል። ኢትዮጵያውያን በጋራ ራዕይ ላይ ከተሰባሰቡ በኋላ፤ ስብራት ለይተን መፍትሔ ማበጀት ያስፈልጋል ሲሉም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የእድገት ጉዞ እና የፖለቲካ ችግር ስብራት የጠላቶቻችን አጀንዳ የሆነው መለያየት ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህ መፈወሻ መድኃኒቱ ደግሞ መደመር ብቻ ነው ሲሉ አስረድተዋል። በጋራ መቆም ብንችል መፍጠን እንችላለን፤ መፍጠር እንችላለን፤ በአስፈላጊው ቦታ ደግሞ መከተል ሳይሆን መዝለል እንችላለን ነው ያሉት።   አክለውም በጋራ ስንቆም ከተቀባይነትና ተከታይነት መላቀቅ እንችላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሐሳብ ተቀብለን፣ ገንዘብ ተቀብለን፣ ተልዕኮ ተቀብለን ኢትዮጵያ ላይ መለማመድ ተገቢ አይደለም በማለት በአጽንኦት ገልጸዋል። በሥነ-ልቦና ስብራት መኖሩንና ጥሩ ነገሮች ሲታዩ የኢትዮጵያ እንደሆነ ያለመቀበል ተገቢነት የሌለው ልምምድ መኖሩንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እንደምትችል እና በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኗን መቀበል እንደሚገባም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መክረዋል።
የመደመር መንግሥት ከትናንት እስረኝነት የተላቀቀና ለምክንያታዊነት ትኩረት የሰጠ ነው
Sep 17, 2025 109
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት ከትናንት እስረኝነት የተላቀቀና ለምክንያታዊነት ትኩረት የሰጠ መሆኑን በመደመር መንግሥት መጽሃፍ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀረቡ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በመደመር እሳቤ የጻፉት 4ኛው መጽሃፍ ''የመደመር መንግሥት'' ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። በመጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመጽሃፉ ደራሲና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል። በመጽሃፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር ዳኛቸው አሰፋ(ዶ/ር)፣ መጽሃፉ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ችግሮች ላይ ንደፈ ሃሳባዊ ትንተና ብቻ ሳይሆን ተግባራዊ ምላሽ የሚያመላክት መሆኑንም አብራርተዋል።   ለችግሮች አውዱን የተገነዘበ ሙሉ መፍትሄ ማስቀመጥ እንደሚገባ በመጽሃፉ በግልጽ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ይህም አንድ መንገድን ብቻ ከሚከተል የርዕዮት እስረኝነት የተላቀቀ አካሄድ ነው ብለዋል። መጽሃፉ የያዛቸው ትንተናዎች በምክንያታዊነት ላይ ያረፉና ለምክንያታዊነት ክፍት መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል። መጽሃፉ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የት እንዳለችና መጻኢ ጉዞዋ ምን መምሰል እንዳለበትም በግልጽ ያስቀምጣል ነው ያሉት። በተጨማሪም በዜጎች መካከል መተባበርና መደጋገፍ እንዲኖር መንገድ በማሳየት ሰላምና አብሮነት እንዲጎለብት ዝርዝር ሃሳብ ማስቅመጡንም አንስተዋል።   ሌላኛው በመጽሃፉ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀረቡት የፖለቲካ ተንታኙ ዘሪሁን ተሾመ በበኩላቸው፤ መጽሃፉ ትናትን በልኩ የሚገነዘብና በትናንት እሳቤ ላይ ያልቆመ ስለመሆኑ አብራርተዋል። የዛሬ ችግሮችን በተገቢው መንገድ እንደሚዳስስ ጠቅሰው፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች የተሻለ ነገን ከመገንባት የሚያስቆሙ እንዳልሆኑ በግልጽ እንደሚያመላክትም ነው ያነሱት። በመጽሃፉ የተዳሰሱ ሃሳቦችም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ የሚበጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
የመደመር መንግስት መጽሃፍ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰና መፍትሄ ያመላከተ ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Sep 17, 2025 139
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግስት መጽሃፍ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰና መፍትሄ ያመላከተ ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጻፈው የመደመር መንግስት መጽሃፍ ዛሬ ለንባብ በቅቷል። በመጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ላይ ፕሬዝዳነት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመጽሃፉ ደራሲና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል። በመጽሐፍ ላይ ዳሰሳ ካቀረቡት መካከል የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ እንዳሉት፣ መጽሃፉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሁኔታ የሚያስቃኝ ነው።   በተለይ የኢትዮጵያ ችግሮችን በጥልቅ የዳሰሰ እና ተግባራዊ መፍትሄዎችን ያመላከተ መሆኑንም ተናግረዋል። መጽሃፍ አስተሳሰብ ላይ ትኩረት አድርጎ ከቁጭት እንደሚነሳ ጠቅሰው፣ ይህም ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ነው ያብራሩት። መጽሃፉ ነገሮችን አፍርሶ ከመስራት ይልቅ አዎንታዊውን ማስቀጠል፣ አሉታዊውን ደግሞ ማስተካከልን እንደሚያመላክትም አንስተዋል። ይህም ኢትዮጵያ ለዘመናት የሄደችበትን ተቸካይ የፖለቲካ አካሄድ የቀየረ አተያይ ስለመሆኑም አብራርተዋል። መጽሃፉ ፖለቲካችን ያሸነፈ አካል እንደፈለገ ሁሉን ይጠቅልል ከሚል አካሄድ የሚያወጣ ነው ብለዋል። ''እኔ የፈለኩት ካልሆነ'' ከሚል የዜሮ ድምር ጨዋታ መውጣት የሚቻልበትን ዘመናዊ የፖለቲካ አካሄድ ያመላከተ ስለመሆኑም አቶ ጌታቸው አብራርተዋል። በሌላ በኩል ዜጎች ከመሰረታዊ ፍላጎት ባሻገር በክብር የመኖር ህልማቸውን ለመመለስ አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ችግሮች በነበረው አካሄድ ትርጉም ባለው መልኩ መፍታት እንደማይቻል አንስተው፣ የመደመር እሳቤ ተግባራዊ ያደረገው መፍጠርና መፍጠን በዚህ ረገድ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማን የተከማቸ ችግር ለመፍታት የተተገበረው የመፍጠርና መፍጠን መፍትሄ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ መሆኑንም ተናግረዋል። አዲስ አበባን ለመለወጥ የተጀመረው ስራ አዲስ የስራ ባህልን ያለማመደ መሆኑንም ገልጸዋል። በቀጣይ በአዲስ አበባ የታየው አዲስ ተስፋ ወደ ሁሉም የኢትዮጵያ አቅጣጫ እንዲሰፋ መረባረብ ይገባል ነው ያሉት። መጽሃፉ ለማንበብ ምቹ በሆነ አቀራረብ መዘጋጀቱን የተናገሩት አቶ ጌታቸው፣ ሁሉም እንዲያነበውም ጥሪ አቅርበዋል።
ማህበራዊ
ለህፃናትና ጨቅላ ህፃናት የሚሰጡ የጤና አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል
Sep 17, 2025 45
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡-ለህፃናትና ጨቅላ ህፃናት ከውልደት ጀምሮ የሚሰጡ የጤና አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ማስገኘታቸውን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የዓለም የህሙማን ደህንነት ቀን "ደህንነቱን የጠበቀ የጤና ክብካቤ ለሁሉም ጨቅላ ህፃናት እና ህፃናት "በሚል መሪ ሃሳብ በአለርት ሆስፒታል ተከብሯል።   በዚሁ ወቅት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ እንደገለፁት፤ በኢትዮጵያ የህፃናትና ጨቅላ ህፃናትን ደህንነት ለመጠበቅ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል። ለአብነትም የጨቅላ ህፃናትና ህፃናት የጽኑ ህሙማን ክፍል፣ ማሞቂያ ስፍራ እና የህክምና ግብአትን ከማሟላት አንፃር በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ነው ያነሱት። ከውልደት ጀምሮ የሚሰጡ የህክምና፣ የክትባትና ሌሎች የጤና አገልግሎቶች ደህንነታቸው የተጠበቀ፣ ጥራት ያላቸው እንዲሆኑ መደረጋቸው ለተገኘው ውጤት መሰረት መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣይም የህፃናትና ጨቅላ ህፃናት አገልግሎት በሁሉም ጤና ተቋማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጤና ሚኒስቴር በትኩረት ይሠራል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ናምቢያር ቤጆይ በበኩላቸው፤ የታካሚዎችን ደህንነት መጠበቅና ለህፃናት ከተወለዱበት ቀን ጀምሮ እንክብካቤ በማድረግ ደህንነታቸውን መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።   የአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሽመልስ ገዛኸኝ በበኩላቸው ሆስፒታሉ የህሙማንን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚችሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።   በዚህም ታካሚዎች ወደ ሆስፒታሉ ሲመጡ ደህንነታቸው ተጠብቆ የሚፈልጉትን አገልግሎት በፍጥነት እንዲያገኙ ማስቻሉን ጠቅሰዋል።  
በክልሉ የከተሞችን አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን ፈጣን እድገታቸውን ለማስቀጠል እየተሰራ ነው -አቶ ጥላሁን ከበደ
Sep 17, 2025 49
ዲላ ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የከተሞችን አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን ፈጣን እድገታቸውን የማስቀጠል ሥራ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ገለፁ። በክልሉ በተመረጡ ዘጠኝ ከተሞች የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትን ዲጂታላይዝ የማድረጊያ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዲላ ከተማ እየተካሄደ ነው። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በወቅቱ እንዳሉት በተያዘው አዲስ ዓመት በክልሉ የሚገኙ ከተሞችን ውስብስብ ችግሮች በመፍታት የነዋሪውን እርካታ ለማሳደግ ቅድሚያ ተሰጥቶ ይሠራል።   የኮሪደር ልማት የጎስቋላ ከተሞችን ገፅታ መቀየሩን እንደ አብነት ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ይህንኑ በአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መድገም እንደሚገባም ተናግረዋል። በተለይም በመሬት ልማት፣ በካዳስተር እና በማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ዘርፎች ትኩረት ተደርጎ የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልል ደረጃ በወላይታ ሶዶ እንደሚጀመር አንስተው ይህንንም ወደ ሌሎች ከተሞች ከማስፋት ባለፈ ከዲጂታል ስርዓት ጋር በማቀናጀት ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎትን እውን ለማድረግ እንደሚሠራ ገልፀዋል። በክልሉ በአዲሱ ዓመት በከተሞች ያለውን ውስብስብ አሰራር ለመቀየርና አገልግሎትን የማዘመን ሥራ እየተከናወነ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ ናቸው።   የከተሞችን ፈጣን እድገት የሚመጥን አገልግሎት ለማቅረብ በዘጠኝ የክልሉ ከተሞች የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል። በዛሬው ዕለትም በዲላ ከተማ የተጀመረው ትግበራው በቀሩት ስምንት የክልሉ ከተሞች እንዲቀጥል በማድረግ የከተሞች ተወዳዳሪነት እንዲሰፋ ዕድልን ይፈጥራል ብለዋል። የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው በከተማው የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን በማዘመን የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት እየተሠራ ነው ብለዋል።   በተለይም የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ዲጂታላይዝ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎትን ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል። በኮሪደርና በመሠረተ ልማት ሥራዎች የተመዘገበው ውጤት ይህንን የሚያጠናክር መሆኑንም አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የከተማ ከንቲባዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በባሕርዳር ከተማ  ከአንድ ሺህ  ለሚበልጡ  ተማሪዎች የትምሕርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
Sep 17, 2025 71
ባሕርዳር ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ) ፡- በባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ድጋፍ ለሚሹ ከአንድ ሺህ ለሚበልጡ ተማሪዎች ዛሬ የትምሕርት ቁሳቁስ ተበረከተ። የተበረከተውም ለተማሪዎቹ በነፍስ ወከፍ ለአንድ ዓመት የሚበቃ የደብተር፣ እስክርብቶ፣ እርሳስና ማስመሪያ መሆኑን በርክክቡ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገልጿል።   የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ አስተዳደሩ የበጎ አድራጎት ማሕበራትና ተቋማትን በማስተባበር የትምሕርት ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው። የባሕርዳር በጎ አድራጎት ማሕበርም በ37 ትምሕርት ቤቶች ድጋፍ ለሚሹ ከአንድ ሺሕ ለሚበልጡ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት የሚበቃ የተለያየ የትምሕርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቀዋል።   ከትምሕርት ቁሳቁስ ድጋፍ በተጨማሪ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ከ1 ሺሕ 500 በላይ እማወራና አባወራ ወገኖች የጤና መድሕን አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያገዘ መሆኑንም አንስተዋል።ለተደረገውም ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። የከተማ አስተዳደሩ ትምሕርት መምሪያ ኃላፊ ሙሉዓለም አቤ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የበጎ አድራጎት ማሕበሩ በየዓመቱ የትምሕርት ግብዓት ማሟላት ለማይችሉ ተማሪዎች ድጋፍ ማድረጉ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።   ይሕም ተማሪዎች ለትምሕርት ቁሳቁስ ሳያስቡ ትምሕርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ እንደሚያግዝ ተናግረዋል። ማሕበሩ የትምሕርት ቤቶች ገፅታ እንዲሻሻል ደረጃውን የጠበቀ አምስት ክፍሎች ያሉት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤትና መፀዳጃ ቤቶችን ገንብቶ ማስረከቡንም አንስተዋል። በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 37 የመንግስት ትምሕርት ቤቶች ተማሪዎች የትምሕርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጋቸውን የገለጹት ደግሞ የባሕርዳር በጎ አድራጎት ማሕበር ስራ አስኪያጅ አቶ አሕመድ ይማም ናቸው።   በማዕድ ማጋራት፣ በጤና መድሕን አገልግሎትና በሌሎችም የበጎ አድራጎት ተግባራት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ወገኖች ማሕበሩ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝና አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አብራርተዋል።   የተደረገልኝ የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ትምሕርቴን በአግባቡ እንድከታተልና ውጤታማ እንድሆን ያግዘኛል ያለችው ደግሞ ተማሪ ኃይማኖት ፀጋዬ ናት።
በትምህርት የውጤታማነት ሚስጥሩ ክፍል ውስጥ በንቃት መከታተልና ጠንክሮ ማጥናት ነው
Sep 17, 2025 67
ጅግጅጋ፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- በትምህርት የውጤታማነት ሚስጥሩ ክፍል ውስጥ በንቃት መከታተልና ጠንክሮ ማጥናት መሆኑን በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሶማሌ ክልል ከፍተኛውን ውጤት ያመጣው ተማሪ ሀምዛ ሻም መሐመድ ገለጸ። በሀገሪቷ የተለያዩ አካባቢዎች በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች መኖራቸው ይታወቃል። በዚህም መሰረት በዘንድሮው ፈተና 549 ነጥብ በማምጣት በሶማሌ ክልል ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበው በጅግጅጋ ከተማ ዘ ስፓርክ ትምህርት ቤት የተማረው ተማሪ ሀምዛ ሻም መሐመድ ሆኗል። ለዚህ ውጤት የበቃበትን ምክንያት የኢዜአ ሪፖርተር በጅግጅጋ በመገኘት ተማሪውን አነጋግሮታል። በመጣው ውጤት ደስተኛ መሆኑን የተናገረው ተማሪ ሃምዛ በትምህርት የውጤታማነት ሚስጥሩ ክፍል ውስጥ በንቃት መከታተልና ጠንክሮ ማጥናት መሆኑን ገልጿል። ከሌሎች ተማሪዎች ጋር ሆኖ ጥያቄ በማዘጋጀት እንደሚሰሩና በመምህራኑ የሚሰጡትን የቤትና የክፍል ሥራዎችን በጊዜ ሰርቶ እንደሚያጠናቅቅም ገልጽዋል። መምህራኑ ተጨማሪ የቱቶሪያል ክፍሎች እንደሚያስተምሯቸው ገልጾ፤ ጥሩ የሥነ ልቦና ምክርም እንደሚሰጧቸው ተናግሯል። ተማሪዎች ቤተመጻህፍት በአግባቡ ከተጠቀሙና የሚሰጡ የማጣቀሻ ምንባቦችን (ጋይድላይኖችን) በርትተው ካነበቡ ውጤታማ እንደሚሆኑም መክሯል። በግል ጥረቴ ለስኬት ከመትጋቴም ባለፈ የመምህራኖቼ እገዛና የወላጆቼም ድጋፍ ያልተለየኝ በመሆኑ ውጤታማ ሆኟለሁ ብሏል ተማሪ ሀምዛ። የአሁኑ ውጤት ማምጣት ብቻ በቂ ባለመሆኑና በቀጣይ ብዙ ፈተናዎች ይኖራሉ ያለው ተማሪው በአሸናፊነት በስኬት ለመዝለቅ መዘጋጀቱን አረጋግጧል። በጅግጅጋ የዘ ስፓርክ ትምህርት ቤት ዘንድሮ ያስፈተናቸውን 25 ተማሪዎች በሙሉ ማሳለፍ የቻለ መሆኑም ታውቋል።      
ኢኮኖሚ
በመደመር እሳቤ የህዳሴን ግድብ የመሰሉ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ለማሳካት ትብብራችንን ልናጠናክር ይገባል
Sep 17, 2025 34
ሚዛን አማን፤ መስከረም 7/2018 (ኢዜአ)፡- በመደመር እሳቤ የህዳሴን ግድብ የመሰሉ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ለማሳካት በትብብር መንቀሳቀሱ ሊጠናከር እንደሚገባ ተመላከተ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሚዛን አማን ከተማ የታላቁን ሕዳሴ ግድብ መመረቅ ተከትሎ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄዷል። በሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ መሠረተ ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጅዮ ሳፒ እንዳሉት፤ በመደመር እሳቤ የህዳሴን ግድብ የመሰሉ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ለማሳካት ትብብራችንን ልናጠናክር ይገባል።   ለዚህም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የፈጠረውን መነቃቃት በሁሉም አካባቢ ሊጎለብትና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን ለማሳካት ሊውል ይገባል ብለዋል። ''የደምና የላብ ዋጋ የተከፈለበት የጋራ አሻራችን የሆነው ሕዳሴን መድገም ቀጣዩ ራእያችን ይሆናል'' ሲሉ ገልጸዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በበኩላቸው ወደ ሥልጣኔ ማማ ለመድረስ የተፈጥሮ ሀብታችንን አልምቶ መጠቀም መጀመራችን ትልቅ ትርጉም አለው ብለዋል።   የብልጽግና ጉዞ አመላካች የሆነው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከልማት ባሻገር የአገራዊ መግባባት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። አንድነታችን ፈተናን መሻገርያ ምርኩዛችን በመሆኑ የማይቻሉ የሚመስሉ ጉዳዮችን ችለን ለዓለም ማሳየታችንን መቀጠል አለብን ነው ያሉት። በይቻላል መንፈስ ግንባታው ተጠናቆ ወደ ኢኮኖሚ ምንጭነት የተቀየረው ዓባይ ታሪክ ከመናገር ታሪክ ወደ መሥራት እንድንሸጋገር አድርጎናል ያሉት ደግሞ የሚዛን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰሎሞን ሌዊ ናቸው።   በሰልፉ ላይ ከተገኙት የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ተስፋዬ ማሞ የግድቡ መመረቅ የመቻል ምልክት መሆኑን ተናግረዋል።   ሁሉም ኢትዮጵያውያን ላለፉት 14 ዓመታት ካላቸው ቀንሰው እያዋጡ አንድነታቸውን ያጸኑበት መሆኑን ገልጸው በቀጣይ መንግሥት የሚያስጀምራቸውን ፕሮጀክቶች በተሻለ መልኩ ለመደገፍ አነሳስቶናል ብለዋል።   ወይዘሮ ብርሃኔ ወርቁ በበኩላቸው በመተባበር የጀመርነው የሕዳሴ ግድብ መመረቁ፤ ጀምሮ ለመጨረስ አንድነት ትልቅ አቅም መሆኑን አረጋግጠዋል።
ማህበረሰቡ ስለ ታክስና ጉምሩክ ስርዓት ያለውን ግንዛቤ  ለማሳደግ የቅንጅት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Sep 17, 2025 56
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡-ማህበረሰቡ ስለ ታክስና ጉምሩክ ስርዓት ያለውን ግንዛቤ ለማሳደግ የቅንጅት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ ገለፁ። "የታክስና ጉምሩክ እውቀት ለህግ ተገዢነት መሰረት ነው" በሚል መሪ ሀሳብ በታክስና ጉምሩክ ዙሪያ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ የተማሪዎች የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዷል።   የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ በዚሁ ወቅት የማህበረሰቡን የታክስ ግንዛቤ ለማሳደግ ስትራቴጂክ እቅድ ተነድፎ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። በኢትዮጵያ የታክስ እና ቀረጥ አከፋፈል ላይ የህግና አሰራር ስርዓት ማሻሻያ በማድረግ በርካታ ለውጦች መመዝገባቸውን አንስተው፥ ይህንን አስፍቶ ለማስቀጠል የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልዶች ላይ ስለ ታክስ ሀገራዊ ፋይዳ በቂ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የውድድሩ ተሳታፊና አሸናፊ ተማሪዎች ያገኙትን የታክስ እውቀት ለትምህርት ቤት ጓደኞቻቸውና ለአካባቢያቸው ማህበረሰብ ተደራሽ እንዲያደርጉ አፅንኦት ሰጥተዋል። ከዚህ አኳያ ከትምህርት ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ተተኪው ትውልድና ማህበረሰቡ የታክስና ጉምሩክ ስርዓትን በተመለከተ ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ የቅንጅት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በበኩላቸው ማህበረሰቡ ስለታክስና ጉምሩክ በቂ ግንዛቤ ኖሮት ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣ ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።   በታክስና ጉምሩክ ስርዓት ዙሪያ በተዘጋጀው ሀገራዊ ውድድር ከ320 በላይ ትምህርት ቤቶች ከ14 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንደተሳተፉበት ገልጸዋል። በቀጣይ ሁሉም ባለድርሻ አካል ግንዛቤ የማስፋትና ህገወጥነትን የመከላከል ሃላፊነትን በአግባቡ እንዲወጣ ጠይቀዋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስክ ሦስተኛ የወጡት ተማሪዎች በበኩላቸው፥ ስለታክስና ጉምሩክ በተሰጣቸው ስልጠና በቂ ግንዛቤ መቅሰማቸውን ተናግረዋል። የግንዛቤ መፍጠሪያና የውድድር መርሃ ግብሮች ተጠናክረው መቀጠላቸው ትውልዱ ስለ ታክስ ሀገራዊ ፋይዳ በቂ እውቀት እንዲኖረውና ሀገሩን በታማኝነት እንዲያገለግል ያስችላሉ ብለዋል።   የታክስና ቀረጥ ህግን ለማስከበር፣ ህገወጥነትን ለመከላከልና ግንዛቤን ለማስፋት የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ጠቁመዋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለወጡ ተማሪዎች፣ ለአሰልጣኝ መምህራን እና ለትምህርት ቤቶች የተለያዩ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።
የታላቁ የህዳሴ ግድብ ስኬት በቀጣይ ለሚከናወኑ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መሠረት የጣለ ነው
Sep 17, 2025 35
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ስኬት በቀጣይ ለሚከናወኑ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መሠረት የጣለና ኢትዮጵያ በሀብቷ የመጠቀም መብቷን በተግባር ያረጋገጠችበት መሆኑን የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ ገለጹ። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን በማስመልከት የድጋፍ እና የደስታ መግለጫ ሰልፍ "በአንድነት አሳክተናል" በሚል መሪ ሃሳብ በቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል። የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን በጋራ ያሳኩት እና የኢትዮጵያን ማንሰራራት ያሳየ ነው። ታላቁ የህዳሴ ግድብ በርካታ ውጣ ውረዶችን በማለፍ ለስኬት መብቃቱን ገልፀው፤ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የራሱን አሻራ ያሳረፈበት መሆኑን አስታውሰዋል። የታላቁ የህዳሴ ግድብ ስኬት በቀጣይ ለሚከናወኑ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መሠረት የጣለና ኢትዮጵያ በሀብቷ የመጠቀም መብቷን በተግባር ያረጋገጠችበት መሆኑን ተናግረዋል። በድጋፍ ሰልፉ ከተሳተፉት መካከል ወይዘሮ ሙሉ ሊኪሳ እንዳሉት ኢትዮጵያውያን በጋራ ከቆምን ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በመስራት ከድህነት መውጣት እንደምንችል አሳይተናል ብለዋል።   ወጣት ቢኒያም ግርማ በበኩሉ የህዳሴ ግድብ ስኬት በሌሎች አገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ በጋራ በመቆም የበኩላችንን እንድንወጣ የሚያነሳሳን ነው ሲል ተናግሯል። ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ ደረጄ ቶሌራ በበኩሉ ህዳሴ ግድብን በጋራ ማሳካት እንደቻልን ሁሉ ሌሎች አገራዊ ፕሮጀክቶችን በትብብር ማስቀጠል አለብን ብሏል።   የግድቡ ስኬት እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶቻችንን ለልማት እንድናውል ትልቅ መነሳሳት ፈጥሮብናል ሲል ነው ሃሳቡን የገለጸው። የህዳሴ ግድብን በራሳችን አቅም መገንባት መቻላችን ለዘመናት ቁጭታችን ፍጻሜ የሰጠ ነው ሲሉ የገለጹት ደግሞ በሰልፉ የተሳተፉት አባገዳ አዲሱ በልዳ ናቸው። አቶ ደጀኔ አስፋው በበኩላቸው፤ጫናዎችን በመቋቋም ህዳሴ ግድብን በራስ አቅም ማጠናቀቃችን ለሌሎች የልማት ስራዎች ትምህርት ይሆነናል ብለዋል።   አስተያየት ሰጪዎቹ በህዳሴ ግድብ ግንባታ የነበራቸውን ተሳትፎ በሌሎች ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ በመድገም ለሀገር ዕድገት መሰረት የሚሆን ተሳትፎ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።  
የደብረ ብርሃን ከተማ ልማትን ለማስቀጠል ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ ትኩረት ተደርጓል
Sep 17, 2025 37
ደብረብርሃን ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፡- የደብረ ብርሃን ከተማን የንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ ትኩረት መደረጉን የከተማው አስተዳደር ገለጸ። የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች መምሪያ በ2017 ዓ.ም እቅድ አፈፃፀምና የ2018 ዓ.ም የገቢ እቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ አካሂዷል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በመድረኩ ላይ እንደገለጹት የደብረ ብርሃን ከተማ በኢንዱስትሪ፣ ኢንቨስትመንትና ሌሎች ልማቶች ተመራጭ እየሆነች መጥታለች። ''በቀጣይም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አቅደን ለመፈጸም ገቢን አሟጠን መሰብሰብ ላይ አተኩረን መስራት አለብን'' ያሉት ከንቲባው ''በራስ አቅም የከተማችንን እድገት ለማፋጠንና የህዝባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ ይሰራል'' ብለዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ አቶ አበባየሁ ሞገስ በበኩላቸው የከተማዋን ልማት ለማፋጠን በ2018 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል።   ከሀምሌ ወር ጀምሮ በተካሄደው የደረጃ “ሐ” ግብር ስርአት 64 ሚሊየን ብር መሰብሰቡን ጠቁመው የተጠናከረ የገቢ የማሰባሰብ ስራ እየተካሄደ ነው ብለዋል። ህብረተሰቡም የቫት ደረሰኝ በመቀበልና ነጋዴዎችም ደረሰኝ በአግባቡ በመቁረጥና ሌሎች ህጋዊ አሰራሮችን በመከተል ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። የጠባሴ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሲራክ ጌታነህ፣ ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል። የአፄ ዘራያቆብ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈፃሚ አቶ ወንድወሰን እሸቴ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ ከህብረተሰቡ የሚነሱ የልማት ስራዎችን መመለስ መቻሉን ተናግረዋል። በዚህ ዓመትም የተጣለውን እቅድ ለማሳካት ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር 12 ሺህ የሚጠጉ ግብር ከፋዮች መኖራቸውን የከተማው ገቢዎች መምሪያ አስታውቋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በቅርቡ 21 የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ወደ ሥራ ይገባሉ - የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
Sep 16, 2025 186
አዲስ አበባ፤ መስከረም 6/2018(ኢዜአ)፦ በቅርቡ 21 የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ወደ ሥራ እንደሚገቡ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አስታወቀ። በፌዴራል ደረጃ በመሶብ የአንድ ማዕከል የሚሰጡ አገልግሎቶች 180 መድረሳቸውም ተገልጿል። የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የመንግስት አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም አንድ አካል የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተገልጋዮችን ቅሬታና እንግልት በመቀነስ ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው።   የመንግስት አስተዳደርንና አገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻል ዘመናዊ ሲቪል ሰርቪስ ለመገንባት መንግስት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት። በአንድ ማዕከል የሚሰጡ አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል መንገድ ሲሆን፤ ለአገልግሎት አሰጣጡ የራሱ ልኬት ተቀምጦለታል ብለዋል። አንድ ብሎ የጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እየተስፋፋ መምጣቱን አመልክተው፤ ይህም እስከ መስከረም 2018 ዓ.ም መጨረሻ ማዕከላቱን 21 በማድረስ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት እንዲሰጡ ይደረጋል ብለዋል። በኢትዮጵያውያን የበለጸገውና አገልግሎቶቹን የሚያስተሳስረው ቴክኖሎጂ አስተማማኝ መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉንም ነው ኮሚሽነሩ የተናገሩት። በመላ ሀገሪቱ ቢያንስ አንድ የመሶብ አገልግሎት እንዲኖር እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕከላቱን በክልሎች የማስፋፋት እቅድ መኖሩንም ገልጸዋል። በፌዴራል ደረጃ 180 የደረሰው የአገልግሎቶች አቅርቦት በክልሎች ከፍተኛው 50 ዝቅተኛው ደግሞ 10 መሆኑንም አንስተዋል። እንደኮሚሽነሩ ገለጻ፣ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በርካታ ተገልጋዮች ደስተኛ መሆናቸውንና ይህም የመልካም አስተዳደርና የብልሹ አሰራር ችግሮችን በመፍታት በኩል ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል ነው ያሉት። የማዕከሉን አገልግሎቶች በማስፋት የተገልጋዩን እርካታ የበለጠ ለማሳደግ እንደሚሰራም ነው ኮሚሽነሩ ጨምረው ያረጋገጡት።
ህብረተሰቡ የቴሊግራምና የዋትሳፕ አካውንቶች ላይ ካነጣጠሩ አጭበርባሪዎች መጠንቀቅ አለበት
Sep 14, 2025 322
አዲስ አበባ፤ መስከረም 4/2018(ኢዜአ)፦ ህብረተሰቡ የቴሊግራምና የዋትሳፕ አካውንት ተጠቃሚዎች ላይ ካነጣጠሩ አጭበርባሪዎች ሊጠነቀቅ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አሳሰበ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ባስተላለፈው የጥንቃቄ መልዕክት እንደገለጸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገራችን የቴሌግራምና ዋትሳፕ ተጠቃሚዎች ላይ ያነጣጠረ የማጭበርበርና የአካውንት ነጠቃ እንቅስቃሴዎች እየጨመሩ መጥተዋል። ከሰሞኑም ከዚህ ቀደም ከነበረው በተለየ ሁኔታ የግለሰቦች የቴሊግራምና ዋትሳፕ አካውንቶች በመረጃ መንታፊዎች በከፍተኛ ደረጃ እየተነጠቁና ማጭበርበሮች እየተፈጸሙ ስለመሆኑ በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የሳይበር አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ ማዕከል/Ethio-CERRT/ ማረጋገጥ ችሏል። እነዚህ የአካውንት ነጠቃዎች የሚፈጸሙት ለጥቃት ኢላማ ላደረጉት አካል አጥፊ ተልዕኮ ያላቸውን ሊንኮች በመላክና ሊንኩን እንዲከፍቱ የሚያደርጉ ቴክኒኮችን በመጠቀም መሆኑንም አስታውቋል። ከነዚህ ቴክኒኮች መካከል በጣም ወሳኝ በሆነ ጉዳይ አስቸኳይ በዙም ወይም በሌሎች የኦንላይን ፕላትፎርሞች ስብሰባ ስለሚኖር በተላከው ሊንክ አማካኝነት እንዲሳተፉ በመደወልና በማግባባት ሲሆን ሊንኩን ከፍተው በሚገቡበት ወቅት አካውንታቸውን ይነጥቃሉ ብሏል። ከዚህ የአካውንት ነጠቃ በኋላ የተነጠቀውን የቴሊግራም ወይም ዋትሳፕ አካውንት በመጠቀም ወደ ግለሰቡ ወዳጆች ለወሳኝ ጉዳይ ገንዘብ እንደሚያስፈልጋቸዉና እንዲያስገቡላቸዉ በጽሁፍ መልዕክት በመጠየቅ እያጭበረበሩ እንደሚገኙም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ገልጿል። በመሆኑም የቴሌግራምና ዋትሳፕ ተጠቃሚዎች ከማታውቁት አካል አጓጊ የሆኑና አስቸኳይነት ያላቸው ሊንኮች ሲላክልዎት እንዲሁም ሊንኩን እንዲከፍቱ ጥሪ ሲደርስዎት አካውንትዎን ለመጥለፍ ሊሆን ስለሚችል ሊንኮችን ከመክፈት በመቆጠብ ከፍተኛ ጥንቃቄ ልታደርጉ ይገባል ብሏል። ከዚህ ባሻገር የቴሌግራምና የዋትሳፕ ተጠቃሚዎች ከወዳጅ ዘመድ ወይም የስራ ባልደረባ በእነዚህ አካውንቶች ለሚቀርብ የብድርና የድጋፍ ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት በፊት ወደ ጠያቂው ስልክ ደውሎ ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር አሳስቧል።
ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Sep 10, 2025 428
ሀዋሳ፤ ጳጉሜን 5/2017(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ከወረቀት ነጻ አገልግሎት በመስጠት እንደ ሀገር ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ። “ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ” በሚል መሪ ሀሳብ የነገው ቀን በሲዳማ ክልል ደረጃ በሀዋሳ ተከብሯል።   የሲዳማ ክልል መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ አስፋው ጎኔሶ በመርሀግብሩ ላይ እንዳሉት በክልሉ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። በክልሉ በሀዋሳ የአንድ መሶብ አገልግሎትን ለማስጀመር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል። ለዚህም በርካታ ተገልጋይ ያላቸው አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ተመርጠውና ለስራ ምቹ የሚሆን ህንጻ ተዘጋጅቶ የኔትወርክ ዝርጋታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። የአንድ መሶብ አገልግሎቱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሚሰጥበት ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመዋል። የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ሀላፊ አቶ አሰፋ ጉራቻ በበኩላቸው እንደገለጹት በክልሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ከወረቀት ነጻ የሆነ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማምጣት በትኩረት እየተሰራ ነው።   ህብረተሰቡ ለእንግልት የሚዳረግባቸውን አገልግሎቶች በመለየት በአንድ ማዕከል ውስጥ ያለ ውጣውረድ በኦን ላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል ። የመሶብ አገልግሎቱ ትልቅ ፋይዳ እንዳለውና ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎችን እንደሚያግዝ ጠቁመዋል። የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ በራሶ የዲጂታል አገልግሎቱን በተሳካ ሁኔታ ለማስጀመር እንዲቻል የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀት ያለው ትውልድ መፍጠር ዋና ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   ለዚህም በኮደርስ ኢትዮጵያ እስካሁን ከ30 ሺህ በላይ የክልሉ ነዋሪዎች ስልጠና እንዳገኙ ጠቁመው እንደ ሀገር ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማሳካት በክልሉ ቢያንስ 50 በመቶ የመንግስት ሰራተኛው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀት እንዲኖረው ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል። “ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ” በሚል መሪ ሀሳብ በተከበረው የነገው ቀን በዓል ላይ በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ተጠሪ የሆኑ ተቋማትና ኤጀንሲዎች ሰራተኞች ተገኝተዋል።
በኦሮሚያ ክልል የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን በዲጅታል ቴክኖሎጂ በማስደገፍ ፈጣንና ቀልጣፋ እንዲሆን እየተደረገ ነው
Sep 10, 2025 352
አዳማ፤ ጳጉሜን 5/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን በዲጅታል ቴክኖሎጂ በማስደገፍ ፈጣንና ቀልጣፋ እንዲሆን እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል። በዛሬው የ"ነገው ቀን" መርሃ ግብር "ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ" በሚል መሪ ሀሳብ የአዳማ ከተማ አስተዳደር የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን አስጀምሯል። በከተማ አስተዳደሩ አገልግሎቱን ያስጀመሩት በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ፣ የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) እና የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኃይሉ ጀልዴ ናቸው።   በዚህ ወቅት በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ እንደገለጹት፤ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ በማሻሻል መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ለዲጂታል ኢትዮጵያ እውን መሆን ወሳኝ ነው። ዲጂታል ኢትዮጵያ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በመተግበር ግልጸኝነትንና ተጠያቂነትን መዘርጋት ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል። በዛሬው እለት አገልግሎቱ አዳማን ጨምሮ በቢሾፍቱ፣ ሸገር እና ሻሸመኔ ከተሞች መጀመሩን አስታውቀዋል። በቀጣይም በሁለተኛው ምዕራፍ በበርካታ ከተሞች አገልግሎቱን ማስፋት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከመንግስት አገልግሎት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችንና መልካም አስተዳደርን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ገንቢ ሚና እንዳለው አስረድተዋል። የክልሉ መንግሥት የሕብረተሰቡን ጥያቄ በቅርበት ለመፍታትና የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ለማሻሻል በ5ሺህ ቀበሌዎች ሰራተኞችን በመመደብ አርሶ አደሩ ከቀዬው ሳይርቅ አገልግሎት እያገኘ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት እንቅስቃሴዎችን በማሳለጥ የክልሉ ብሎም የሀገር መንሰራራትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በርካታ ተቋማት ቴክኖሎጂ በመጠቀም አገልግሎታቸውን በማዘመን ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በአዳማ ዛሬ የተጀመረው የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ በዲጅታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ ፈጣንና ቀልጣፋ እንዲሆን እንደሚያስችል አነስተዋል። አገልግሎቱ አስተማማኝና የተሳለጠ እንዲሆን የሰው ኃይልን ለማብቃት ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራም አንስተዋል።   የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው፤ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በአስተዳደሩ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ሙሉ በሙሉ መቀየር ማስቻሉን ተናግረዋል። በዚህም የመሬት አስተዳደር፣ ኢንቨስትመንት፣ ኮንስትራክሽንን ጨምሮ ከ100 በላይ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መንገድ ለተገልጋዩ ሕብረተሰብ መስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል። ይህም የተገልጋዩን እርካታ እና የከተማዋን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ ወሳኝነት እንዳለው አስረድተዋል።
ስፖርት
ብርሃኔ አደሬ - ኢትዮጵያን በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለበርካታ ጊዜ የወከለች አትሌት
Sep 17, 2025 41
ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1983 በፊንላንድ ሄልሲኒኪ ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አንስቶ በተካሄዱት ውድድሮች ላይ በሙሉ ተሳትፋለች። በነዚህ ሻምፒዮናዎች ላይ በርካታ አትሌቶች የኢትዮጵያ ስም እና ባንዲራ ከፍ ያደረጉ ገድሎችን ሰርተዋል። አትሌት ብርሃኔ አደሬ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሲነሳ ሁሌም አብራ እንድትነሳ የሚያደርግ ታሪክ አላት። በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያን በመወከልና ብዙ ጊዜ በመሳተፍ የአጠቃላይ ቀዳሚነቱን ደረጃ የያዘችው ብርሃኔ አደሬ ናት። ብርሃኔ ከእ.አ.አ 1993 እስከ 2005 በተካሄዱ ሰባት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናዎች ላይ ተሳትፋለች። አትሌቷ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው እ.አ.አ በ1993 በጀርመን ስቱትጋርት በተካሄደው አራተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ነበር። በ10000 ሜትር ሴቶች ውድድር ማጣሪያ ተሳትፋ ለፍጻሜው ማለፍ አልቻለችም። በስዊድን ጉተንበርግ እ.አ.አ በ1995 በተካሄደው አምስተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ10000 ሜትር ሴቶች ብትወዳደርም ማጣሪያውን አላለፈችም። ብርሃኔ እ.አ.አ በ1997 በግሪክ አቴንስ በተካሄደው ስድስተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ10000 ሜትር ፍጻሜ ተወዳድራ አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። 31 ደቂቃ ከ49 ሴኮንድ ከ17 ማይክሮ ሴኮንድ ውድድሩን ለማጠናቀቅ የፈጀባት ጊዜ ነበር። በስፔን ሲቪያ እ.አ.አ በ1999 በተካሄደው ሰባተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በድጋሚ በ10000 ሜትር ፍጻሜ ተወዳድራ 31 ደቂቃ ከ29 ሴኮንድ ከ11 ማይክሮ ሴኮንድ ሰባተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። አትሌት ብርሃኔ የመጀመሪያ ሜዳሊያዋን ያገኘችው እ.አ.አ በ2001 በካናዳ ኤድመንተን በተደረገው ስምንተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ነው። አትሌቷ በ10000 ሜትር ፍጻሜ 31 ደቂቃ ከ48 ሴኮንድ ከ85 ማይክሮ ሴኮንድ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። በውድድሩ የወርቅ ሜዳሊያውን ያገኘችው አትሌት ደራርቱ ቱሉ ነበረች። እ.አ.አ በ2003 በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው ዘጠነኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለብርሃኔ ትልቁን ስኬት ያገኝችበት ሆኖ አልፏል። አትሌት ብርሃኔ በ10000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ 30 ደቂቃ ከ04 ሴኮንድ ከ18 ማይክሮ ሴኮንድ የወርቅ ሜዳሊያ አገኝታለች። በርቀቱ የሻምፒዮናውን ክብረ ወሰን አሻሽላለች። በወቅቱ በ5000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ ተሳትፋ 10ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ብርሃኔ የመጨረሻ የሻምፒዮና ተሳትፏዋን ያደረገችው እ.አ.አ በ2005 በፊንላንድ ሄልሲንኪ በተካሄደው 10ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ነበር። በ10000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን ተከትላ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አገኝታለች። 30 ደቂቃ ከ25 ሴኮንድ ከ41 ማይክሮ ሴኮንድ ውድድሩን ለማጠናቀቅ የፈጀባት ጊዜ ነበር። አትሌት ብርሃኔ አደሬ በሻምፒዮናው ተሳትፎ አንድ የወርቅ እና ሁለት የብር ሜዳሊያዎችን አግኝታለች። አትሌቷ በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና እና በአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮናዎች ላይም ኢትዮጵያን ወክላ ተወዳድራለች። ብርሃኔ ራሷን ከውድድር ከማግለሏ በፊት በግማሽ ማራቶን እና ማራቶን ውድድሮች ላይ ተሳትፎ አድርጋለች። አትሌት ብርሃኔ አደሬ እና የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሁሌም ሲወሳ የሚኖሩ የታሪክ ትስስሮሽ አላቸው።
ሲምቦ አለማየሁ እና ሎሚ ሙለታ በ3000 ሜትር መሰናክል ፍጻሜ ላይ ይወዳደራሉ 
Sep 17, 2025 81
አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦ በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በሚደረገው የሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ፍጻሜ ሲምቦ አለማየሁ እና ሎሚ ሙለታ ኢትዮጵያ ወክለው ይሳተፋሉ። ውድድሩ ከቀኑ 9 ሰዓት ከ57 ላይ ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌት ለፍጻሜ ያለፉት በማጣሪያው ጥሩ ብቃት በማሳየት ነው። በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለሶስተኛ ጊዜ እየተሳተፈች የሚገኘው ሲምቦ አለማየሁ እ.አ.አ ጁላይ 5 2025 በአሜሪካን ኢውጅን በተካሄደ ውድድር 8 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ ከ90 ማይክሮ ሴኮንድ በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቷን አስመዝግባለች። ከሁለት ዓመት በፊት በሀንጋሪ ቡዳፔስት በተካሄደው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ3000 ሜትር መሰናል ፍጻሜ ተወዳድራ 13ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። እ.አ.አ በ2022 በአሜሪካ ኢውጅን በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በርቀቱ ባደረገችው ማጣሪያ ወደ ፍጻሜ ሳታልፍ ቀርታለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት ሎሚ ሙለታ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ስትሳተፍ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ቡዳፔስት በተካሄደው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ3000 ሜትር መሰናክል ፍጻሜ ተሳትፎ 12ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። አትሌት ሎሚ እ.አ.አ ኦገስት 6 2024 በፈረንሳይ ፓሪስ በተካሄደው 9 ደቂቃ ከ6 ሴኮንድ ከ7 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቷን አስመዝግባለች። ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተሳትፏቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ሜዳሊያ ለማግኘት ይሮጣሉ። በፍጻሜው ውድድር ላይ ከተለያዩ ሀገራት የተወጣጡ 15 አትሌቶች ይሳተፋሉ። በጃፓን ቶኪዮ እየተካሄደ ባለው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ እስከ አሁን ሁለት የብር እና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ በማግኘት 13ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
አካባቢ ጥበቃ
በአረንጓዴ አሻራ የተተከለውን ችግኝ የመንከባከብ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል
Sep 13, 2025 331
ባሕርዳር፤ መስከረም 3/2018 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከለውን ችግኝ ለውጤት ለማብቃት የመንከባከቡ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ‎‎የቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር እስመለዓለም ምህረት፤ በክረምቱ የተተከለውን ችግኝ የፅድቀት ምጣኔ 85 በመቶ ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል። ለዚህም ሕብረተሰቡ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየአካባቢው የተከለውን ችግኝ ለውጤት ለማብቃት የመንከባከብ ተግባር ማጠናከሩን ገልጸዋል።   ሕብረተሰቡ የችግኝን ጠቀሜታ በየጊዜው በውል እየተረዳ መምጣቱን ገልጸው ከ205 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የተተከለው ችግኝ ከነሐሴ 2017 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ የአረምና የመንከባከብ ተግባር በንቃት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ከእንክብካቤው ጎን ለጎንም በጠፋ ችግኝ የመተካት ተግባርም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ እንደሚገኝም አንስተዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከለው ችግኝ የክልሉን የደን ሽፋን በአንድ በመቶ በማሳደግ ወደ 17 ነጥብ 3 በመቶ እንደሚያደርሰው ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን የሰከላ ወረዳ አርሶ አደር አለሙ ወልዴ በሰጡት አስተያየት፤ በክረምት ወቅት በግልና በወል መሬት የተከሉትን ችግኝ በማረም እየተንከባከቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የችግኝን ጥቅም በአግባቡ እየተረዳን በመምጣታችን የእንክብካቤ ተግባሩን እያከናወንን ያለነው በራሳችን ተነሳሽነትና ፍላጎት ነው ብለዋል።   በአረንጓዴ አሻራ የተከልነው ችግኝ የአፈር መሸርሸር እንዲቀንስ አግዟል ያሉት ደግሞ በደቡብ ጎንደር ዞን የፋርጣ ወረዳ አርሶ አደር ተስፋሁን መንጌ ናቸው። በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት ወረዳ አርሶ አደር ምህረቱ አስማረ፤ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመሆን የተከሉትን ችግኝ ተንከባክበው እያሳደጉ መሆኑን ተናግረዋል። ከግብርና ቢሮው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ ቀደም ባለው ዓመት የክረምት ወቅት በአማራ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከለው ችግኝ በተደረገለት እንክብካቤ 82 በመቶውን ማፅደቅ ተችሏል።
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም እያደረገች ያለው ጥረት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው 
Sep 13, 2025 336
ጂንካ፤ መስከረም 3/2018 (ኢዜአ)ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቋቋም ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያደረገች ያለው ጥረት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ በኢጋድ የክፍለ-አህጉሩ ዳይሬክተር ሙባረክ ማቦያ ገለፁ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) አባል አገራት ተወካዮች በኢጋድ መሪነት በኢትዮጵያ ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች እየተተገበሩ ያሉ ፕሮጀክቶች አፈፃፀምን ተመልክተዋል።   ልዑካኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በና-ፀማይ ወረዳ ድርቅን ለመቋቋም በሚደረገው ሂደት በአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ዘንድ የመጡ ተጨባጭ ለውጦችንም መመልከት ችለዋል። በኢጋድ የክፍለ አህጉሩ ዳይሬክተር ሙባረክ ማቦያ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቋቋም ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያደረገች ያለው ጥረት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው። በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ፣ ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች በመስኖ ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ጥረቶች ውጤት እያስመዘገቡ እንደሆነ መመልከታቸውን ተናግረዋል። እንዲሁም የአርብቶ አደሩን የኢኮኖሚ አቅም ለማሳደግ፣ የእንስሳት ምርታማነትን ለማሻሻል፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋንን ለማሳደግና ድርቅን የሚቋቋም ማህበረሰብ ለመፍጠር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል።   በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በዝርዝር አቅርበው እንደነበር ያስታወሱት ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ ያደረግነው ምልከታም ይህንኑ በተግባር የሚያሳይ ነው ብለዋል። በግብርና ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የድርቅ መቋቋም እና የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም ብሔራዊ አስተባባሪ ጀማል አልዬ፤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቋቋም የተሻለ ውጤት ማምጣቷን ገልጸዋል።   የኢጋድ አባል አገራት በኢትዮጵያ እያደረጉ ያሉት ጉብኝትም ያለውን ልምድና ተሞክሮ ለመቅሰምና በሌሎች የድርጅቱ አባል ሀገራትም ተሞክሮውን ለማስፋት ታስቦ የተደረገ እንደሆነም አስረድተዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኤካል ነትር በበኩላቸው፤ በክልሉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የአርብቶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆኑን አንስተዋል።   በቀጣይም የእንስሳት ጤናን በመጠበቅ፣ ድርቅን አስቀድሞ በመከላከል፣ አርብቶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖ የማይበገር ኢኮኖሚን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ የአደጋ ስጋት ቅነሳና አካታች የኢኮኖሚ እሴት ማሻሻያ ፕሮጀክት አስተባባሪ ስዩም መታፈሪያ (ዶ/ር) ባደረጉት ገለፃ የደቡብ ኦሞ ዞን ዝናብ አጠርና በተደጋጋሚ ለድርቅ ተጋላጭ የሆነ አካባቢ እንደነበር ገልጸው ተጋላጭነቱን ለመቀነስ በተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ገልፀዋል።   ቡድኑ በደቡብ ኦሞ ዞን በና ፀማይ ወረዳ ለመስኖ፣ ለሰውና ለእንስሳት ሁለገብ አገልግሎት የሚሰጠውና 300 ሜትር ጥልቀት ያለው እንዲሁም በፀሐይ ኃይል በሰከንድ 26 ሊትር ውሃ የሚያመነጨውን ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ፕሮጀክትንም ተመልክቷል። ከዚህ በተጨማሪ የእንስሳት ማቆያ እና የእንስሳት የገበያ ማዕከል፣ የከብቶች የመኖ ልማት እና የመኖ ማከማቻ መጋዘንና ሌሎች ፕሮጀክቶችንም ጎብኝተዋል። ልዑካን ቡድኑ በአፋርና በሶማሌ ክልል ምልከታ ያደረጉ ሲሆን ከደቡብ ኢትዮጵያ በመቀጠል ወደ ኦሮሚያ ክልል በማቅናት በቦረና ዞን ምልከታ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል።
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የጀመረቻቸውን ኢንሼቲቮች በደቡብ ደቡብ ትብብር ማጠናከር ይገባል
Sep 12, 2025 379
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የጀመረቻቸውን ኢንሼቲቮች በደቡብ ደቡብ ትብብር ማጠናከር እንደሚገባ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ገለጹ፡፡ የአፍሪካ የበካይ ጋዝ ልቀት መጠን ከአራት በመቶ ባይበልጥም በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ከፍተኛ ተጎጂ መሆኗ አልቀረም፡፡ በተለይም አፍሪካን ጨምሮ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ የሚደርስባቸውን ችግር የህልውና ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ሆኗል፡፡ አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የጎላ በካይ ጋዝ ከሚለቁ ሀገራት ከመጠበቅ የራሷን መፍትሔ መፈለግ አለባት የሚለው የብዙ ዓለም አቀፍ ተቋማት ምክረ ሀሳብ ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር እንደ ቻይና እና ጃፓን በቴክኖሎጂ ከበለጸጉ ሀገራት ጋር በደቡብ ደቡብ ትብብር የቴክኖሎጂ አቅምን ማሳደግ እንደሚገባም ይገልፃሉ፡፡ የዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት ረዳት ዋና ጸሀፊ ቶማስ አሳሬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአየር ንብረት ፋይናንስ በማመንጨት እና ጎረቤት ሀገራት በታዳሽ ኃይል በማስተሳሰር የጎላ አበርክቶ አለው፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቢሊዬን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአመራር ቁርጠኝነት እና የኢትዮጵያ ህዝብ ተሳትፎ የላቀ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም የምታደርገውን ጥረት በደቡብ ደቡብ ትብብር ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡   የዓለም የእርሻና ምግብ ድርጅት ረዳት ዳይሬክተር ጀነራል እና የአፍሪካ ተጠሪ አበበ ኃይለገብርኤል (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስን ከፍተኛ በካይ ጋዝ የሚለቁት ያደጉ ሀገራት እንዲሸፍኑ የወጡ የፓሪስ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በአግባቡ ገቢራዊ አልተደረጉም ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የደቡብ ደቡብ ትብብርን በማጠናከር የቴክኖሎጂ አቅማቸውን ማሳደግ እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡ አፍሪካ የታዳሽ ሀይል፣ እምቅ የማዕድንና ሌሎች የተፈጥሮ ጸጋዎች ያሏት አህጉር መሆኗን በመጥቀስ፤ በደቡብ ደቡብ ትብብር ጸጋዋን የምትጠቀምበት ቴክኖሎጂ ማላመድ አለባት ብለዋል፡፡ በደቡብ ደቡብ ትብብር ማዕቀፍ እንደ ቻይና ያሉ ሀገራት በብዙ ተፈትነው መሰረት የያዘ የቴክኖሎጂ አቅም ገንብተዋል ያሉት ዶክተር አበበ ፤ አፍሪካ ዘግይታ መግባቷን /late comer advantage/ እንደ እድል መጠቀም እንዳለባት ገልጸዋል፡፡
ጉባኤው አፍሪካ ለዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ የመፍትሔ ማዕከል መሆኗን በግልጽ ያሳየ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Sep 10, 2025 446
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 5/2017(ኢዜአ)፦ ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አፍሪካ የመፍትሔና የታዳሽ ኃይል ማዕከል መሆኗን ያሳየችበት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ፡፡ "ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፣ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" በሚል መሪ ሀሳብ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል፡፡ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በመዝጊያ መርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አፍሪካ ግልጽ አቋሟን ያንጸባረቀችበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ተጎጂ ብቻ ሳይሆን በአረንጓዴ ልማትና በታዳሽ ሀይል ዓለም አቀፍ የመፍትሔ ማዕከል መሆኗን አሳይቷል ብለዋል፡፡ ዓላማችን የበለጸገች፣ አይበገሬና አረንጓዴ አፍሪካን መፍጠር ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የኤሌክትሪክ ሃይል የማያገኙ 600 ሚሊዮን አፍሪካውያን መኖራቸው ኢፍትሐዊነት መሆኑን የዓለም ማህበረሰብ ሊገነዘብ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን የመቋቋም ተግባራችን ያለንን ሰፊ ሀብት፣ የታዳሽ ሃይል ልማትና የአየር ንብረት ለውጥ ፍትህ ላይ ማተኮር አለበት ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ያለውን እምቅ የውሃና የጸሀይ ሀይል በመጠቀም ሁሉም ዜጎችና ድርጅቶች የኤሌክትሪክ ሃይል እንዲያገኙ ማድረግ እና በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ አፍሪካውያን በዓለም እንደ ተረጂ የምንታይበትን ትርክት በተባበረ አቅማችን መቀየርና የዓለም የመፍትሔ አካል መሆናችንን ማሳየት ይኖርብናል ብለዋል፡፡ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ለዓለም የሚተርፍ መፍትሔ አላት ያሉት ፕሬዝዳንቱ ቢሊዮን ችግኞች በየዓመቱ የሚተከሉበት የአረንጓዴ ዐሻራ፣ የታዳሽ ኃይል ልማት፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃን በምሳሌነት ጠቅሰዋል። የአዲስ አበባ የመሪዎች ቃል ኪዳን መጽደቅ ትልቅ እርምጃ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ በራሷ አቅም መፍትሔ እንደምታመጣ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የመሪዎች ቃል ኪዳን የታዳሽ ኃይልና የአረንጓዴ ልማትን በማስፋት ነገን መገንባት፣ ወሳኝ ማዕድናትን ጨምሮ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ሀብት በራስ ማስተዳደርና መጠቀም፣ ጥብቅ ደኖችን ጨምሮ የተፈጥሮ ቅርሶቻችንን መጠበቅ ላይ ያተኮሩ ሦስት ምሰሶዎች እንዳሉት አስረድተዋል። የአዲስ አበባ የመሪዎች ቃል ኪዳን በአጭር ጊዜ ዕቅድ ወጥቶለት ሊተገበር የሚገባ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አፍሪካውያን ለአህጉራቸው ሰላም እና ብልጽግና ያላቸውን ቁርጠኝነት ዳግም ሊያረጋግጡ ይገባል - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ 
Sep 9, 2025 520
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2017(ኢዜአ)፦ አፍሪካውያን ለአህጉራቸው ሰላም እና ብልጽግና ያላቸውን ቁርጠኝነት በማጽናት የተሻለ መጻኢ ጊዜን ለመፍጠር በጋራ እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጥሪ አቀረቡ። የአፍሪካ ህብረት ቀን ዛሬ እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ ሴፕቴምበር 9/1999 በሲርት ድንጋጌ አማካኝነት የተቋቋመበት ቀን የሚታወስበት ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ቀኑን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት አፍሪካውያን ቀኑን ሲዘክሩ የአህጉሪቷን ለውጦች በማክበር እና ለአንድነት፣ ሰላምና ብልጽግና ያላቸውን ቁርጠኝነት ዳግም በማረጋገጥ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል። የህብረቱ መመስረት ውሳኔ ለአፍሪካ ትብብር፣ ትስስር እና አጋርነት መሰረት የጣለ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ቀን የጋራ ጉዟችንን፣ የህዝባችንን አይበገሬነት እና ያጋመደንን የፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ የምናከብርበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ በመልዕክታቸው በአፍሪካ በተለያዩ መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶችን አንስተዋል። በሰላምና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና፣ የታዳሽ ኃይል ልማት፣ ዲጂታል ኢኖቬሽንና የወጣቶችን አቅም በመገንባት የተከናወኑ ስራዎች አፍሪካን በዓለም መድረክ ያላት ሚና እንዲያድግ አስተዋጽኦ ማድረጉን ነው ሊቀ መንበሩ የገለጹት። የአፍሪካ ህብረት ለአጋርነት፣ ትስስር እና ዘላቂ ልማት ያለውን ቁርጠኝነት ጠቅሰው መንግስታት፣ ሲቪክ ማህበረሰቡ፣ የግሉ ዘርፍ እና ወጣቱ ፈተናዎችን በጋራ በመሻገር አጀንዳ 2063 ይዞ የመጣችውን እድሎች እንዲጠቀም ጥሪ አቅርበዋል። ሁሉም አፍሪካውያን ክብራቸው ተጠብቆ የሚኖሩባት እና መጻኢ ጊዜያቸው ብሩህ የሆነች አህጉር እጅ ለእጅ በመያያዝ እንገንባ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በአህጉራዊ ትስስር ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Aug 26, 2025 1230
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በአህጉራዊ ትስስር አጀንዳ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰሩ አስታወቁ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት(ጄኔቫ) የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኛ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሴኤ) ዋና ፀሐፊ ክላቫር ጋቴቴ ጋር ተወያይተዋል።   ሁለቱ ወገኖች አፍሪካ በዓለም መድረክ አንድ የጋራ ድምጽ እንዲኖራት ማድረግ ያለውን ወሳኝ ጠቃሜታ አጽንኦት ሰጥተው መክረውበታል። የአፍሪካ ህብረት እና ኢሲኤ በንግድ፣ቀጣናዊ ትስስር እና የአፍሪካ የአዕምራዊ ንብረትን የበለጠ አጀንዳ ማራመድ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።   ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት(ጄኔቫ) የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው በሐምሌ ወር 2017 ዓ.ም መሾማቸው የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ህብረት እና ኢሲኤ ትብብራቸውን እ.አ.አ በ1960ዎቹ መግቢያ ላይ መጀመራቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ።
አፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት በትብብር ይሰራሉ
Aug 24, 2025 1037
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 18 /2017 (ኢዜአ)፦አፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት በትብብር እንደሚሰሩ አስታወቁ። ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም(ቲካድ) በዮካሃማ መካሄዱን ቀጥሏል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከፎረሙ ጎን ለጎን ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ፕሬዝዳንት አኪሂኮ ታናካ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።   የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የጃይካ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንዲሁም ኢኮኖሚና ማህበራዊን ጨምሮ በአፍሪካ ቁልፍ ዘርፎች እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት አድንቀዋል። ሊቀ መንበሩ እና ፕሬዝዳንቱ የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ያላቸውን የጋራ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ዘጠነኛውን የቲካድ ፎረም መንፈስ ወደ ዘላቂ የኢኮኖሚ ለውጥ በጋራ የመፍጠር ምዕራፍ ማሸጋገር እንደሚገባም አንስተዋል። ከነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው ፎረም የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ፤ የአህጉር በቀል መፍትሄዎች መድረክ 
Aug 23, 2025 1073
በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን የአየር ንብረት በርቀት የሚያዩት ስጋት ሳይሆን የዕለት ተዕለት እውነታቸው ነው። በጎርፍ ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች እና ተጠራርገው የሚወሰዱ ንብረቶች፣ በተከታታይ ድርቆች ምክንያት የሚያጋጥመው የምርታማነት መቀነስ የአየር ንብረት ለውጥ ከወለዳቸው ቀውሶች መካከል ይጠቀሳሉ። እነዚህ በተጨባጭ የዜጎችን ኑሮ እየተፈታተኑ ያሉ ችግሮች በአፍሪካ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስነ ምህዳር ላይ ለውጥ እንዲመጣ አስገድደዋል። የድህነት ምጣኔ እና የተፈናቃይ ዜጎች እየጨመረ መምጣት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎችን በተግባር የገለጡ ጉዳዮች ሆነዋል።   አፍሪካ ለዓለም የበካይ ጋዝ ልቀት ከአራት በመቶ በታች ድርሻ ቢኖራትም የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳት ከፍተኛ ቀንበር የሚያርፍባት አህጉር ሆናለች። ከሳህል ቀጣና የበረሃማነት መስፋፋት እስከ ምስራቅ አፍሪካ ኃይለኛ ጎርፎች የአህጉሪቷ ዜጎች በጣም ውስን ድርሻ ባላቸው ጉዳይ የቀውሱ ከፍተኛ ሰላባ እየሆኑ ነው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የአስቸኳይ ጊዜ ውስጥ ናት ቢባል ማጋነን አይሆንም። እንደ ዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት መረጃ ከእ.አ.አ 1991 እስከ 2022 ባለው ሶስት አስርት ዓመታት ባሉ እያንዳዱ አስርት ዓመታት በአፍሪካ በአማካይ የ0 ነጥብ 3 ዲግሪ ሴልሺየስ የሙቀት ጭማሪ ተመዝግቧል። እ.አ.አ በ2024 የዓለም ሙቀት በ1 ነጥብ 2 ዲግሪ ሴልሺየስ ጨምሮ በዓለም ታሪክ ከፍተኛው ሙቀት የተመዘገበበት ዓመት ነበር። 2024 በአፍሪካ የሙቀት መጠን 0 ነጥብ 86 በመቶ በመጨመር በአህጉሪቷ ታሪክ ከፍተኛው ሙቀት የተዘመገበበት ዓመት ሆኖም ተመዝግቧል። ከሙቀቱ በአሳሳቢ ሁኔታ መጨመር ባሻገር ድርቅ፣ ጎርፍ እና የምግብ ዋስትና ስጋት ላይ መውደቅ ሌሎች የአፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ናቸው። እ.አ.አ 2024 ደቡባዊ አፍሪካ ክፍል በቅርብ አስርት ዓመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ድርቅ አጋጥሟታል። በድርቁ ምክንያት ዛምቢያ እና ዚምባቡዌ የሰብል ምርታቸው በ50 በመቶ ቀንሷል። በምስራቅ እና ማዕከላዊ አፍሪካ በቅርብ ጊዜ የተከሰቱ ከባድ ጎርፎች ሚሊዮኖችን አፈናቅለዋል፤ የዜጎች ህይወት አመሰቃቅላዋል መሰረተ ልማቶችንም አውድመዋል። የዓለም አቀፉ ሜትሮሎጂ ድርጅት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካን ከሁለት እስከ አምስት በመቶ ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) ወጪ እየወሰደ ይገኛል። አንዳንድ ሀገራት ለአየር ንብረት አስቸኳይ ምላሽ ዘጠኝ በመቶ ጥቅል ሀገራዊ ምርታቸውን ፈሰስ ያደርጋሉ። አፍሪካ በየዓመቱ ከ30 እስከ 50 ቢሊዮን ዶላር ለአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ አቅዶች ትግበራ ቢያስፈልጋትም ከዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ ውስጥ የምታገኘው ገንዘብ ከአንድ በመቶ በታች ነው። የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት የ2024 የአፍሪካ ሪፖርት የአፍሪካ የግብርና ምርታማነት ከእ.አ.አ 1961 በኋላ በ34 በመቶ መቀነሱን ይገልጻል። የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ ሀገራት ምግብ ለመግዛት የሚያወጡት 35 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ወጪ እ.አ.አ በ2025 ማብቂያ ወደ 110 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ከፍ እንደሚል ገልጿል። የበረሃማነት መስፋፋት፣ የብዝሃ ህይወት መመናመን፣ የጤና እክሎች፣ መፈናቀል እና የታሪካዊ ቅርሶች አደጋ ላይ መውደቅ አፍሪካ እየገጠሟት ያሉ የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎች ውጤት ናቸው። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት በየዓመቱ 250 ቢሊዮን ዶላር ቢያስፈልጋትም እያገኘች ያለችው 30 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ስጋት አፍሪካ የጥያቄ አምሮት ኖሮባት የምታነሳው አጀንዳ ሳይሆን የፍትህ እና የህልውናዋ ጉዳይም ጭምር ነው። በአዲስ አበባ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፥ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አህጉሪቷ እየገጠሟት ካሉ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይመክራል። የሀገራት መሪዎች፣ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ወጣቶች እና የግሉ ዘርፍ በአንድነት ይወያያሉ። በጉባኤው ላይ አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በታዳሽ ኢነርጂ፣ ዘላቂ ግብርና እና ተፈጥሮ ተኮር መፍትሄዎች ጨምሮ በአፍሪካ ያሉ አረንጓዴ የመፍትሄ ሀሳቦች የበለ ማላቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሀገራት ተሞክሯቸውን ያቀርባሉ። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ በየዓመቱ የሚያጋጥማትን የ220 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ አቅርቦት ክፍተት መሙላት እና አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም ላይ ምክክር ይደረጋል። በብራዚል ቤለም በሚካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ 30) ጨምሮ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ድርድሮች ላይ የአፍሪካን ፍላጎቶች እና ጥቅሞች ማስጠበቅ የሚያስችል የጋራ እና ጠንካራ አቋም መያዝ ከጉባኤው የሚጠበቅ ውጤት ነው። የአፍሪካ ሀገራት በጉባኤው ላይ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል የሚያስችሉ ተጨባጭና መሬት ላይ የወረዱ እቅዶቻቸው ላይ የሚያቀርቡ ሲሆን የገቡትን ቃል ኪዳን ወደ ተግባር መቀየራቸውን የሚከታተል የቁጥጥር ስርዓት ትግባራትን የሚያጠናክሩባቸው መንገዶችን በማቅረብ በአጠቃላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ቃልኪዳናቸውን ዳግም ያድሳሉ።   አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች ገፈት ቀማሽ ሳትሆን የመፍትሄዎች እና የአይበገሬነት ስራዎች ማሳያም ናት። የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ እና አከባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የኬንያ የእንፋሎት እና የፀሐይ ኃይል ኢንሼቲቮች እንዲሁም የሞሮኮ ኑር ኦውርዛዛቴ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አረንጓዴ ልማት ሊሆን የሚችል ብቻ ሳይሆን በተጨባጭ የሚሳካ መሆኑን አፍሪካ ማረጋገጫ እንደሆነች በግልጽ የሚያመላክት ነው። አፍሪካ ከዓለም ዋንኛ በካይ ጋዝ ለቃቂ ሀገራት ገንዘብ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ሀገር በቀል የፋይናንስ እና ሀብት ማሰባሰብ አቅማቸውን የበለጠ ማሳደግ ይጠበቅባታል። የአዲስ አበባው ጉባኤም የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ አቅርቦታቸውን እንዲጨምሩ ጥሪ የሚቀርብበት ነው። አፍሪካውያን እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ ከንግግር ያለፉ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን በመተግበር አይበገሬ አቅም ሊገነቡ ይገባል። የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ሀገር በቀል የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎችን ከዓለም አቀፍ አጋርነት ጋር ከማዛመድ አኳያ ያላው ሚና ወሳኝ የሚባል ነው። ጉባኤው አፍሪካ ከአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ትርክት ወደ መፍትሄ አፍላቂነት እና የግንባር ቀደም ሚና አበርካችነት ለመሸጋገር እንደ መስፈንጠሪያ የሚያገለግል ትልቅ እድል ነው። የአዲስ አበባው ጉባኤ ከስብስባ ባለፈ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ቆርጣ ለተነሳችበት የተግባር ምላሽ ጉዞ እና የዓለም አቀፍ ተጠያቂነት መረጋገጥ የጋራ ትግል ውስጥ ትልቅ እጥፋት ሊሆን ይችላል።  
ሐተታዎች
ከጉባ እስከ ዓለም መድረክ፤ የዓለም አይኖች ያረፉበት የሕዳሴ ግድብ 
Sep 13, 2025 398
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም መመረቁ ይታወቃል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ (ዶ/ር)፣ የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦመር ጊሌህ፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ (ዶ/ር)፣ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት፣ የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ አሞር ሞትሊ፣ የእስዋቲኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሴል ሚሶ ድላሚኒ፣ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ፣ በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ተገኝተዋል።   የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዓለምን ዓይን የሳበው የአፍሪካ ግዙፉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ በመሆኑ ብቻ አይደለም። ፕሮጀክቱ የአፍሪካን ህልሞች፣ ትብብር እና ቀጣናዊ ትስስር መልህቅ በመሆንም ጭምር ነው። የምረቃት ስነ ስርዓቱ ከአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ፣ አውሮፓ እና በተቀረው ዓለም በሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ዓለም አቀፍ ሽፋን አግኝቷል። ቢቢሲ በዘገባው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያንን በአንድነት ያቆመ የሀገር ኩራት ማሳያ መሆኑን ገልጾ የግድቡ ስኬት የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የዓመታት ጥረትና ድካም፣ በዜጎች የሀብት፣ የጉልበት እና የገንዘብ አስተዋፅኦ የተገኘ ውጤት መሆኑን አመልክቷል። ግድቡ ለሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን ህይወት እንደሚለውጥ ትልቅ ተስፋ እንደተጣለበትም አመልክቷል። ግድቡ የኢትዮጵያውያን ኩራት እና የቀጠናዊ ትብብር ማሳያ መሆኑን አበይት ጭብጡ አድርጎ ዘገባውን የሰራው ዶቼ ቬሌ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ የገንዘብ መዋጮ የተገነባው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች ታላቅ ስኬት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መግለጻቸውን አንስቷል። ግድቡ የተፋሰሱ ሀገራት የኢኮኖሚያዊ ውህደት እና ትብብር መሰረት መሆኑን የጠቀሰው የጀርመኑ መገናኛ ብዙሃን፤ ግድቡ፣ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሌላቸው ኢትዮጵያውን የኢነርጂ አቅርቦትን ከማረጋገጡ ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጿል። የተርኪዬ ዜና አገልግሎት አናዶሉ የሕዳሴ ግድቡን አስመልክቶ በሰራው ዘገባ የግድቡ ምረቃ ታሪካዊ ድል ሲል በዘገባው ላይ አስፍሯል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ከቅኝ ግዛት ዘመን ጀምሮ የነበረውን ኢፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀም የቀየረ መሆኑን ጠቅሶ ኢትዮጵያ የአፍሪካን ትልቁን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ እውን ማድረግ መቻሏን ጠቅሷል። አልጄዚራ የኢትዮጵያውያን የዘመናት ህልምን እውን ያደረገ ስኬት ነው ሲል በሰራው ዘገባ ያለምንም አይነት የውጭ እርዳታና ድጋፍ ፣በኢትዮጵያውያን የገንዘብ መዋጮና የቦንድ ግዢ መገንባቱ የግድቡን ስኬት የተለየ እንደሚያደርገው ገልጿል። በዜጎች ዘንድ ከፍተኛ የባለቤትነት ስሜትና የጋራ ኩራት የፈጠረ ፕሮጀክት መሆኑን ያመለከተው ዘገባው፤ ኢትዮጵያውያን የገጠማቸውን ፈተና አልፈው ያጠናቀቁት ግድብ የሀገራዊ አንድነት ማሳያ እና የትውልድ ቅብብሎሽ ውጤት እንደሆነም አንስቷል። ሲኤንን የሕዳሴው ግድብ ምረቃ ሀገራዊ ኩራት ምንጭ ሆኗል ያለ ሲሆን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትልቁን የኤሌክትሪክ ሀይል ማመነጫ ግድብ መሆኑንና ለሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ከማረጋገጡ ባለፈ የሀገር ኩራት ምንጭ መሆኑን ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የግድቡ አላማ ወንድም ሀገራትን መጉዳት ሳይሆን ለቀጣናው ብልጽግናን ማምጣት እንደሆነ መግለጻቸውንም በዘገባው ላይ አስፍሯል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መመረቅ ኢትዮጵያን የቀጠናው የኃይል ማዕከል ያደርጋታል ያለው ደግሞ አሶሲዬትድ ፕሬስ ነው። ኢትዮጵያ የአፍሪካን ትልቁን የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ስትመርቅ፣ ፕሮጀክቱ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በማሳደግ ለኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋፅኦ ከማድረጉ ባሻገር ጎረቤት ሀገራት ኃይል ለመግዛት የሚችሉበትን ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቅሷል። ታላቁ የሕዳሴው ግድብ መመረቅ ኢትዮጵያን የቀጣናው የኃይል ማዕከል ያደርጋታል ያለው ደግሞ አሶሲዬትድ ፕሬስ ነው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ትልቁን የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ስትመርቅ፣ ፕሮጀክቱ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ በማሳደግ ለኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋፅኦ ከማድረጉ ባሻገር ጎረቤት ሀገራት ከኢትዮጵያ ኃይል ለመግዛት እንደሚያስላቸው ነው በዘገባው ያመለከተው። የቻይናው ዢንዋ የሕዳሴው ግድብ ምረቃ የሀገራዊ ስኬት ማሳያ እንደሆነ ጠቅሶ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ትልቁ የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነውን ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በይፋ መርቃለች ሲል ገልጿል። በስነ ስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፕሮጀክቱ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንደሚያጠናክር፣ የተረጋጋ የኃይል አቅርቦትን እንደሚያረጋግጥና የቀጠናዊ የኃይል ትስስርን እንደሚያሳድግ መግለጻቸውን ዘግቧል። በምረቃው ላይ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች መገኘት የፕሮጀክቱን ቀጣናዊ ፋይዳ የሚያሳይ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የጎረቤቶቿን ጥቅም ሳይጎዳ በጋራ እድገት ላይ ያላትን ቁርጠኝነት በድጋሚ ማረጋገጣቸውን አውስቷል። አጠቃላይ ዘገባዎቹ የሕዳሴ ግድብ በቀጣናው፣ በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን የገዘፈ ተጽእኖ የሚያሳይ ነው። የሕዳሴ ግድብ ምርቃት ከመገናኛ ብዙሃን ባለፈ በዓለም ደረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦችን ትኩረት ስቧል። የአሜሪካ የቅድሞ ቅርጫት ኳስ ተጫዋች እና ታዋቂው የቲክቶክ የይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ የሕዳሴ ግድቡ ምርቃትን በአፍሪካ የተሰራ አዲስ ታሪክ ሲል ገልጾታል። ግድቡ በዓለም ላይ ከሚገኙ 20 ግዙፍ የኤሌትሪክ ማመንጫ ግድቦች አንዱ መሆኑንና ለወደፊት የኢትዮጵያን መጻኢ ጊዜ ብሩህ የሚያደርግ እንደሆነ ተናግሯል። ሕዳሴ የኢትዮጵያ ኢነርጂ ምርት በእጥፍ በመጨመር ሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ ያስችላል ብሏል። ግድቡ የሚያመነጨው ኃይል ለኢንዱስትሪ እና ማኑፋክቸሪንግ እድገት ትልቅ ሚና እንዳለው የገለጸው ዲላን የጎረቤት ሀገራት ኤሌክትሪክ በሽያጭ እንዲያገኙ ብር የሚከፍት እንደሆነም ጠቅሷል። ከ17 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ የቲክቶክ ተከታይ ባለው የዲላን ፔጅ ገጽ የተላለፈው መልዕክት ይህ ጽሁፍ እስከጠናከረተበት ሰዓት 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሰው ቪዲዮውን በመውደድ( ላይክ በማድረግ) ድጋፉን ገልጿል። በቲክቶክ ገጹ ላይ በጤና እና መዝናኛ ቪዲዮቹ የሚታወቀው የአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል የቀድሞ አባል ካጋን ዱንላፕ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት በኢትዮጵያ የኢነርጂ እና የመሰረተ ልማት ዘርፍ ትልቁ የሚባል ስኬት እንደሆነ ገልጿል። ግንባታው 14 ዓመታት የፈጀው ይህ ግዙፍ የሃይድሮ ፓወር ፕሮጀክት በራስ አቅም የተገነባና ይህም የብሄራዊ ጥረት ውጤትና የኢነርጂ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ መሆኑን አመልክቷል። ይህ የዱንላፕ ቪዲዮ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተከታይ ባለው የቲክቶክ ገጹ ላይ እስከ አሁን ከ165 ነጥብ 6 ሺህ በላይ ተመልካች አይቶታል። ኬንያዊቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ ብሪላ ናታሻ በቲክቶክ ገጿ ባስላለፈችው የቪዲዮ መልዕክት አፍሪካ በሕዳሴ ግድብ ታሪክ ሰራች ስትል ገልጻለች። የአፍሪካ የነጻነት ምድር የሆነችው ኢትዮጵያ ያለ ምንም የውጭ እርዳታ በኢትዮጵያውያን ገንዘብ እና ትልቅ መስዋዕትነት ማሳካቷን ተናግራለች። ኢትዮጵያ ግድቡን በራሷ እቅም መገንባቷ አፍሪካ መሰል ግዙፍ ፕሮጀክቶችን የማንንም እጅ ሳትጠብቅ መስራት እንደምትችል በግልጽ ለዓለም መልዕክት ያስተላለፈችበት ነው ብላለች። የግድቡ ምርቃት አፍሪካ በራሷ አቅም የራሷን ጉዳይ ለመፈጸም የወሰደችው ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጠቅሳ ምርቃቱ ድንቅ የሚባል ዜና እንደሆነ ተናግራለች። የቲክቶክ ገጿ ላይ 189 ሺህ 500 ተከታይ ያላት ናታሻ ግድቡን አስመለክቶ ያስተላለፈችው መልዕክት እስከ አሁን ባለው መረጃ 33 ሺህ 800 ሰዎች በመውደድ አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ከዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እና ተጽኦ ፈጣሪ ግለሰቦች ሀሳብ ወጣ ስንል የግድቡ ምርቃት የአፍሪካ የአይበገሬነት እና የጽናት ምልክት፣ ራስን የመቻል እና የቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ትብብር መገለጫ ሆኖ የታየበት ነው። የምስራቅ አፍሪካ መሪዎች በምርቃቱ ላይ መገኘት የአፍሪካ ፕሮጀክት የሆነው ሕዳሴ ግድብ ኢኮኖሚን በመቀየር፣ የኢነርጂ ዋስትናና ደህንነት በማረጋገጥ እና ድንበር ተሻጋሪ የዲፕሎማሲ ትስስር መጋመጃ መሆኑም ታይቶበታል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካ የራሷን እጣ ፈንታ በራሷ የመወሰን አቅም እንዳላት የሚያሳይ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በግድቡ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ገልጸዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ትልቅ ታሪካዊ አንድምታ አለው ያሉ ሲሆን አፍሪካውያን የራሳቸውን የብልጽግና መሻት በራሳቸው ማካሳት እንደሚችሉም የሚያመላክት መሆኑን አመልክተዋል። የሕዳሴ ግድብ ከብሄራዊ ፕሮጀክትነት ባለፈ የፓን አፍሪካ አቅምን በተግባር ያሳየና የአፍሪካ መር መሰረተ ልማት ግንባታ መገለጫ ነው ያሉት ሩቶ ግድቡ በቀጣናው ለሰላም እና ብልጽግና ያለንን የጋራ ህልም ማሳካት በእጃችን ያለ ጉዳይ መሆኑን የሚያሳይ ነው ብለዋል። በግድቡ ምርቃት ላይ የተገኙት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አህጉራዊ ትብብርና ግንኙነትን የሚያጠናክር የወንድማማችነት ምልክት እንደሆነ ተናግረዋል። የላይኛውና የታችኛው ተፋሰሱ ሀገራት መበልጸግ የሚችሉት በጋራ እንደ አንድ ማህበረሰብ በመስራት መሆኑን ገልጸው፤ ውሃና ሌሎች ተፈጥሯዊ ሀብቶች በድንበር የተወሰኑ ሳይሆኑ የወደፊት እጣ ፈንታችንን የሚያስተሳስሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል። የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት የሕዳሴ ግድቡ መመረቅ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የኩራት ቀን ነው ያሉ ሲሆን ግድቡ የኃይል ፍላጎትን ከማሳካት ባለፈ ለልጆቻችን የምንመኘውን የበለጸገ ሀገርና አህጉር ለማስረከብ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን ፕሮጀክት ነው ያሉት ደግሞ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ናቸው። ግድቡ የዓለምን ሕዝብ ያስደነቀ የአፍሪካ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሐሙድ አሊ ዩሱፍ ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ገንብታ ለምረቃ ያበቃችው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከሀገሬው አልፎ ለጎረቤት ሀገራት ብርሃን ነው ሲሉ ገልጸዋል። የዚህ ፕሮጀክት ስኬት ከአኅጉራዊ አጀንዳዎች ጋር የሚጣጣም መሆኑን በመጥቀስ፤ ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ በመገንባት ኢትዮጵውያንን እና ቀጣናውን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በራስ አቅም የገነባችው በመሆኑም፤ የሚደነቅና ለአኅጉራችን መነሳሳትን የሚቸር ተግባር ነው ብለዋል። 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት የሚያመነጨው ሕዳሴ በየቤቱ ብርሃንን በመስጠት፣ ለኢንዱስትሪዎች አለኝታ በመሆንና ከምስራቅ አፍሪካ ባሻገር እድገትን ለማሳለጥ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። የሕዳሴ ግድብ ከዲፕሎማሲ አኳያ የአፍሪካ መር ስኬትን በግልጽ የሚያመላክት ነው። ግድቡ በኢትዮጵያውያን የራስ አቅም መገንባቱ አፍሪካ የራሷን የልማት መንገድ በራሷ የመወሰን አቅም እንዳላት የሚያመላክትም ነው። ግድቡ ኢትዮጵያ እና የተፋሰሱ ሀገራት በትብብርና በውይይት አማራጭ የውሃ ሀብትን ለጋራ ልማት እና እድገት መጠቀም እንደሚቻል በግልጽ ያሳዩበት ነው። የዓለም አቀፍ መገናኘ ብዙሃንን ከፍተኛ ትኩረት የሳበው የሕዳሴ ግድብ ምርቃት የዜና ዘገባዎች ግድቡ የክፍፍል ሳይሆን የአፍሪካ አንድነት እና ለውጥ ተስፋ መሆኑ ተንጸባርቋል። ፍሪካ በአጀንዳ 2063 ሁሉን አቀፍ እድገት እና ዘላቂ ልማትን እውን ለማድረግ እየተጋች ይገኛል። ሕዳሴ ግድብ ከዚህ አህጉራዊ ማዕቀፍ አንጻር ትልቅ አህጉራዊ ስኬት ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግድቡ መብራትን የሚያበራ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን የመልማት አቅም የሚያስመነድግ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። ዓለም የሕዳሴ ግድብ የራስን መቻል፣ የአይበገሬነት፣ የለውጥ እና መጻኢ ጊዜን ብሩህ የማድረግ ተምሳሌት እንደሆነ በግልጽ መስክሯል።  
ከ500 በላይ ሥራዎችን የሚያሳልጠው ጉበት … 
Sep 1, 2025 860
ጉበት ከ500 በላይ ሥራዎችን የሚያከናውን ዋነኛ እና ሁለገብ የሰውነታችን አካል ነው ይላሉ በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የጨጓራ፣ አንጀት እና ጉበት ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር አብዲ ባቲ። የጉበት ተግባራት በአራት ዐቢይ ክፍሎች እንደሚከፈሉም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። 👉 የመጀመሪያው ተግባሩ፤ ጎጂ ንጥረ ነገሮችን ከደም ውስጥ ማጽዳት፣ ቆሻሻ ምርቶችን ማስወገድ፣ የመድኃኒቶችን ሜታቦሊዝም ማከናወን፣ ከምንበላው፣ ከምንጠጣው እና ከምንተነፍሰው ሁሉ መርዞችን ማስወገድ ነው ይላሉ። 👉 እንዲሁም ሁለተኛው ተግባሩ፤ ቫይታሚኖችን፣ ማዕድናትን እና ኃይልን ማከማቸት መሆኑን ገልጸው፤ ለሰውነታችን ማበረታቻ ኃይል በሚያስፈልግበት ጊዜ ዝግጁ ማድረግ ነው ብለዋል። 👉 ሦስተኛው ተግባር ደግሞ፤ ለደም መርጋት እና ኢንፌክሽኖችን ለመዋጋት ፕሮቲኖችን ማመንጨት መሆኑን ያስረዳሉ። 👉 አራተኛው ተግባሩን ሲያብራሩም፤ ‘Bile’ የሚባል ንጥረ ነገር በማምረት ከሚወዷቸው (ከሚመገቧቸው) ምግቦች ውስጥ የሚገኘውን ስብ እንዲፈጭ ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል። ጉበትን ለህመም የሚያጋልጡ መንስኤዎች ምንድን ናቸው? • እንደ ዶክተር አብዲ ገለጻ፤ ጉበት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ያለው ወሳኝ የሰውነት አካል እንደመሆኑ ለብዙ አደጋዎች ይጋለጣል። ከነዚህ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ ናቸው ብለዋል። 👉 እንደ ሄፓታይተስ ቢ እና ሲ ባሉ ቫይረሶች በደም፣ በመርፌ ወይም ወሊድ ወቅት የሚተላለፉ፤ 👉 ከመጠን በላይ አልኮል መጠቀም፤ 👉 ከመጠን በላይ መወፈር ፤ 👉 የስኳር በሽታ፤ 👉 ከእፅዋት እና የተለያዩ እህሎች (ለምሳሌ ከማሽላ እና በቆሎ) ውስጥ የሚገኙ እንደ አፍላቶክሲን ያሉ መርዛማ ንጥረ ነገሮች ይገኙበታል ብለዋል። 👉 በተጨማሪም ከ40 ዓመት በላይ መሆን፣ በቤተሰብ የሚተላለፉ የጉበት በሽታዎች መኖር፣ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እና አደገኛ ልማዶች ለጉበት በሽታ ከሚያጋልጡ መንስዔዎች መካከል ናቸው ይላሉ። ከእነዚህ አጋላጭ መንስኤዎች አብዛኛዎቹ ሊወገዱ የሚችሉ እንዲሁም ቀድመን በማወቅ እና በመጠንቀቅ መከላከል የሚቻሉ ናቸው ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። ጉበትን በቀላል እና ጤናማ በሆኑ ልምዶች እንዴት ማበረታታት ይቻላል? • በየዕለቱ በቂ ንጹህ ውኃ በመጠጣት፤ • ጤናማ አመጋገብ በመከተል (እንደ ፍራፍሬ፣ አትክልት፣ ጤፍ፣ ባቄላ እና ዓሣ በመመገብ)፤ • ከመጠን በላይ ስብን እና ስኳርን በመቀነስ፤ • አካላዊ እንቅስቃሴን በማዘውተር፤ • አልኮልን በመገደብ ወይም በጭራሽ ባለመጠቀም፤ • የሄፓታይተስ ክትባት በመውሰድ፤ • ያልተረጋገጡ እፅዋትን ከመጠቀም በመቆጠብ፤ • መድኃኒት ከመውሰድ በፊት የጤና ባለሙያ በማማከር እንዲሁም የግል እና የምግብ ንጽህናን በመጠበቅ የጉበትን ጤንነት መጠበቅ ይቻላል ብለዋል ዶክተር አብዲ። ሕክምናውን በተመለከተ o ዶክተር አብዲ እንዳሉት፤ አብዛኛዎቹ የጉበት በሽታዎች ሊታከሙ ይችላሉ፤ በጊዜ ከተደረሰም መቆጣጠር እና መዳን ይችላሉ። o ለሄፓታይተስ ቢ/ሲ ፀረ-ቫይረስ መድኃኒቶች ሕክምና መከታተል፤ o አልኮል መጠጣት በማቆም ጉበት በፍጥነት እንዲያገግም ማገዝ፤ o ለሰባ ጉበት፣ ለስኳር በሽታ እና ለኮሌስትሮል መብዛት በመድኃኒት ማከም፤ o አመጋገብን ማስተካከል፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፤ o የከፋ ደረጃ ላይ የደረሰ ከሆነ እንደደረጃው የተለያዩ ሕክምናዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ እስከ ንቅለ ተከላ ድረስ ሊታከም ይችላል ብለዋል። ጉበት በዓለም አቀፍ ደረጃ…. 👉 በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ 2 ቢሊየን የሚጠጉ ሰዎች እንደ ሄፓታይተስ ቢ እና ሲ ያሉ የጉበት ህመሞች ተጋላጭ ናቸው። ለዚህም ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣት፣ ውፍረት እና የስኳር በሽታ በሰፊው በዓለም አቀፍ ደረጃ ብዙዎችን ተጋላጭ ያደርጋሉ ነው ያሉት። 👉 በአፍሪካ ውስጥ ወደ 80 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች ለሄፓታይተስ ቢ በሽታ ተጋላጭነት ውስጥ ይኖራሉ። ከዚህ ውስጥ 60 በመቶው የሚሆነው በክትባት ውስንነት፣ በጤና አጠባበቅ ተደራሽነት እና በአፍላቶክሲን የተበከሉ (እንደ በቆሎ እና ማሽላ ባሉ) ሰብሎች ምክንያት ለአደጋ ተጋላጭ ነው ብለዋል። 👉 በኢትዮጵያም እስከ 7 በመቶ ያህሉ ሕዝብ ለሄፓታይተስ ቢ ተጋላጭ መሆኑን ነው ያመላከቱት። ለዚህም አልኮል አላግባብ መጠቀም፣ ጫት መጠቀም እና የስኳር በሽታ መጨመር ለብዙዎች በተለይም ከ40 ዓመት በላይ ለሆኑ ወንዶች ተጋላጭነትን እንደሚጨምር አስገንዝበዋል። 👉 በአጠቃላይ ክትባት በመውሰድ፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ በመከተል፣ ጤናማ አመጋገብ በማዘውተር ብሎም በወቅቱ በመታከም ተጋላጭነትን በመቀነስ የጉበት ጤንነትን መጠበቅ ይገባል ሲሉ መክረዋል።
አስም-የበርካቶች ሰቀቀን …
Aug 28, 2025 903
በወቅትና የአየር ሁኔታ ሳይገደብ የበርካቶች ስቃይ የሆነውን አስም እንዴት ማከም ይቻላል…? የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • አስም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ፍጹም ገለጻ፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም አስም ይባላል። • የአስም ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው? የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ በአብዛኛው ምልክቶቹ በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ ገልጸዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸው፤ ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር) ብናኝ፣ የእንስሳት ፍግ ሽታዎች አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ያስረዳሉ። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑን አስረድተዋል። • ለአስም ህመም አጋላጭ ወይም ለህመሙ መባባስ መንስኤዎቹ ምንድን ናቸው? አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የአየር ብክለት፣ ጭስ)፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ዶክተር ፍፁም ገልጸዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ በቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ ወቅት ሙቀት የሚሰጡ ልብሶችን መልበስ፤ ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። • ሕክምናውስ ምንድን ነው? የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የአየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል።
አሸንዳ- የፍቅርና የሰላም አጀንዳ
Aug 23, 2025 1087
በአማረ ኢታይ የሴቶች በተለይም የልጃገረዶች በዓል መሆኑ የሚነገርለት የአሸንዳ በዓል ለማክበር አመቱ እስከሚደርስ ድረስ በጉጉትና በናፍቆት ይጠበቃል። አሸንዳ ይዋቡበታል፣ ቁንጅና ጎልቶ ይወጣበታል፣ ልጃገረዶችና ሴቶች ተሰባስበው የሚያዜሙበት፣ በስጦታ ጭምር የሚታጀብ ልዩ እና ውብ የአደባባይ በዓል ነው። የአሸንዳ በዓል ሲቃረብ በተለይ ልጃገረዶች ቀደም ብለው የመዋቢያ ጌጣጌጦችንና አልባሳትን አዘጋጅተው የበዓሉን መድረስ ይጠባበቃሉ። እለቱም ሲደርስ በተለየ ሁኔታ ተውበውና ደምቀው ከበሮ ይዘውና በጣእመ ዜማ ታጅበው ወደ አደባባይ በመውጣት ያከብሩታል።   በዚህም መሰረት ትግራይ የአሸንዳ በዓል በየዓመቱ ከነሃሴ 16 ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በደማቅ ስነ ስርአት ይከበራል። እለቱ የልጃገረዶች የነፃነት ቀንም በመሆኑ የቤተሰብ፣ የዘመድ አዝማድ ቁጣ እና ይህን አድርጊ ይህን አታድርጊ የሚል ትእዛዝ እና ጫና አይኖርም። በመሆኑም አሸንዳ - የነፃነት፣ የፍቅርና የሰላም አጀንዳ ያነገበ በመሆኑ ከልጅ እስከ አዋቂ በየአመቱ በጉጉት የሚጠበቅ ደማቅ በዓል ነው። የአሸንዳ ልጆች ከበዓሉ ዋዜማ ጅማሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ በየሰፈራቸው በቡድን በቡድን ተሰባስበው የሚጫወቱበት በመሆኑም የህብረት፣ የፍቅር፣ የሰላምና የአብሮነት ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል።   ወላጆቻቸው አነስተኛ ገቢ ያላቸው ልጃገረዶችም ከእኩዮቻቸው፣ ከዘመድ አዝማድ እና ከጎረቤቶቻቸው የመዋቢያ ጌጣጌጦችን፣ አልባሳትና ሌሎች ቁሶችን ወስደው በዓሉን በደስታ የሚያሳልፉ ይሆናል። በዚህም መሰረት በዓሉ የመረዳዳት፣ የትብብርና ችግርን በመተጋገዝ ማለፍ እንደሚቻል የሚያመላክት ልዩ በዓል ነው። በዚሁ መሰረት የ2017 ዓ.ም የአሸንዳ በዓል በደማቅ ስነ ስርአት በመከበር ላይ ይገኛል። የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች፣ በርካታ ቱሪስቶች ልጃገረዶችና ሌሎችም የበዓሉ ታዳሚዎች በተገኙበት በመከበር ላይ ነው። በክብር እንግድነት በመገኘት ንግግር ያደረጉት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፤ ኢትዮጵያ በርካታ ውብ የሆኑ መገለጫዎች ያሏት ሀገር በመሆኗ አጉልተንና ለዓለም አስተዋውቀን የውበታችን ማሳያ እና የሃብት ምንጭ ጭምር ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል። የአሸንዳ በዓልን እሴት በመጠበቅ ለትውልድ ለማስተላለፍ ተቀናጅተን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የሚከበሩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን በማክበር ጠብቆ ማዝለቁ እንዳለ ሆኖ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን የማልማትና ታሪካዊ ቅርሶችን መጠበቅም ትኩረታችን ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል።   በመጨረሻም የአሸንዳ በዓልን በድምቀት እያከበረ ለሚገኘው ለመላው የትግራይን ህዝብ በተለይም ለልጃገረዶች የሰላምና የፍቅር በዓል እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል። "የአሸንዳ በዓልን ማስዋብና ማድመቅ ለሰላምና ለአንድነት ያለንን መልካም ፍላጎትና ምኞት ማሳያ ነው። ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና እንዲለማ እንሰራለን።" በማለት መልእክታቸውን ያጋሩት ደግሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ናቸው። በጊዜያዊ አስተዳደሩ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አፅበሃ ገብረእግዛብሄር በበኩላቸው፣ ባህላዊ ይዘት ያለው የአሸንዳ በዓል ሳይበረዝ ትውፊቱን ጠብቆ እንዲቀጥል የክልልና የፌዴራል መንግስታት በጋራ እንሰራለን ብለዋል። በመቀሌ ከተማ እየተከበረ ባለው የአሸንዳ በዓል ከባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ በተጨማሪ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እና ሌሎችም ታድመዋል። አሸንዳ - የነፃነት፣ የፍቅርና የሰላም አጀንዳ ሆኖ መከበሩንም ቀጥሏል።
ትንታኔዎች
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 675
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 1593
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 1807
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 4998
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 4973
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 3827
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 5336
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 52262
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 49340
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 30150
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 27616
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 24988
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 23299
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 23208
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 22916
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 52262
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 49340
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 30150
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 27616
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የሀመሯ እናት- የደስታ እንባ
Sep 11, 2025 474
የሀመሯ እናት- የደስታ እንባ በጣፋጩ ሰለሞን (ከጂንካ) በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኘው ሐመር ወረዳ የሐመር ብሔረሰብ ዘመን በተሻገሩ ባህላዊ ሥርዓቶች ይታወቃል። በዚህ አካባቢ ከሚዘወተሩትና በብዛት ከሚታወቁት ባህላዊ ሥርዓቶች መካከል “ኢቫንጋዲ እና ኡኩሊ” የተባሉ ባህላዊ ጨዋታዎች ይጠቀሳሉ። “ኡኩሊ”በሐመሮች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ባህላዊ ጨዋታ ሲሆን ለአቅመ አዳም የደረሰና ከብት ለመዝለል ዝግጁ የሆነ የሐመር ወጣት የሚጠራበት የማዕረግ ስም ነው፡፡ “ኡኩሊ” ከብት በሚዘለልበት ዕለት ሥርዓቱ በሚፈጸምበት ሥፍራ ላይ በቅርብም ይሁን በሩቅ ያሉ የወጣቱ ዘመዶች ተጠርተው የሚከናወን ባህላዊ ሥርዓት መሆኑ ይታወቃል። “ኢቫንጋዲ” ደግሞ በሐመሮች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ባህላዊ ጭፈራ ሲሆን ትርጉሙም “ኢቫን” ማለት “ ማታ” ሲሆን “ጋዲ” ማለት ደግሞ “ጭፈራ” ማለት መሆኑ ይነገራል። ኢቫንጋዲ በአዝመራና በደስታ ወቅት በሥራ የደከመን አእምሮና አካል ለማዝናናት ሲባል የሚከናወንና የሀመር ወጣቶች በጉጉት የሚጠብቁት ባህላዊ ጭፈራ ነው። በዚህ ባህላዊ ጨዋታ ላይ የሐመር ወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች አምረውና ተውበው በጨረቃ ብርሃን ይጨፍራሉ። የኢቫንጋዲ ጭፈራ በሶስት ቀን አንድ ጊዜ በሐመር መንደሮች በምሽት ከጨረቃ ድምቀት ጋር አብሮ ይደምቃል። “በጨረቃ ብርሃን አየኋት በማታ ኢቫንጋዲው ቦታ” የተባለላቸው የሃመር ውብ ልጃገረዶችም ከጨረቃ ብርሃን ጋር ደምቀው የሚታዩበት ዕለት ይሆናል። በወጣትነታቸው በዚሁ ባህላዊ ሥርዓት ያለፉት የሀመሯ እናት- ወይዘሮ ባሎ ኡርጎ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ እናት ናቸው። በሐመር ወረዳ ዲመካ ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ ባሎ፤ በደሳሳ ጎጇቸው ሲያገኙ በልተው ሲያጡ ደግሞ ኩርምት ብለው ያሳለፉባቸው ጊዜያት እንዳሉ ያስታውሳሉ። በደሳሳ ጎጆ እየኖሩ ዝናብ ሲመጣ የጎርፍ፣ ብርድና ዶፉ ስጋት ላይ ጥሏቸው እንደኖሩ ያነሳሉ፤ በበጋ ወራት ደግሞ የሚነፍሰው ነፋስና ሀሩሩ ጸሃይ ይፈትናቸው እንደነበር ይናገራሉ። ከእለታት አንድ ቀን ወጣቶችና ጎልማሶች ጭምር ሰብሰብ ብለው መጥተው “ቤትዎን በነፃ ልናድስልዎት ነው ሲሉኝ አላመንኳቸውም ይላሉ። የእውነታችሁን ነው አልኳቸው? አዎን ቤትዎን አፍርሰን ልንሰራልዎት ነው” ብለው አረጋገጡልኝ በማለት ሁኔታውን በደስታ እንባ ታጅበው ያስታውሳሉ። በተባለው መሰረትም በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የቤታቸው እድሳት ተጀምሯል። የኢዜአ ሪፖርተር በስፍራው ተገኝቶ ወይዘሮ ባሎን ባነጋገራቸው ወቅት “ሰው በሚያስፈልገኝ ጊዜ ሰዎች ሁነው የተገኙ ወገኖቼ ችግሬን ለመፍታት በአካል ተገኝተዋል፤ በጣም ደስ ብሎኛል፤ የመኖርን ተስፋ እንድሰንቅ አድርገውኛል በማለት ደስታቸውን በእንባቸው ጭምር ታጅበው ገልጸዋል። የሀመሯ እናት ቤታቸው በፍጥነት ታድሶ የሚረከቡ፣ በቀጣይም አስፈላጊው እገዛና ድጋፍ የሚደረግላቸው መሆኑን የቤቱን እድሳት ያስጀመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኤካል ነትር አረጋግጠዋል። እንደ ወይዘሮ ባሎ፤ ያሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችን የማገዝና የመደገፍ ሃላፊነት አለብን ያሉት ሃላፊው፤ የመረዳዳትና የመተጋገዝ ባህል ጎልቶ እንዲቀጥል ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል። የቢሮው የማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች ለወገኖቻቸውያላቸውን አለኝታነት በተግባር በማሳየታቸውም አመስግነዋል። የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ፤ የዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ ተቋማት፣ግለሰቦች፣ወጣቶችና አዛውንቶች ሳይቀር የተሳተፉበት እና የበርካቶችን ችግር መፍታት የተቻለበት መሆኑን ተናግረዋል። የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች የወይዘሮ ባሎን ቤት ለማደስ በመምጣታቸው አመስግነው፤ ለሌሎች ተቋማትም አርአያ የሚሆን የመልካምነት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ በተያዘው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ቤቶችን ጨምሮ የዞኑን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም በዞኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችን የመደገፍና ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን በስፋት የማከናወን ተግባር በተጠናከረ መለኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የአባይ የቁጭትና የወቀሳ ጊዜ አበቃ!  
Sep 9, 2025 457
የአባይ የቁጭትና የወቀሳ ጊዜ አበቃ! (በቀደሰ ተክሌ - ከሚዛን አማን) አኩርፎ ከቤት ቢወጣ ለመመለስ ሸምጋይ አጥቶ በሰው ሀገር ተንከራታች ልጓም አልባ ሆኖ የኖረው አባይ ከኢትዮጵያ አፈር፣ ማእድናትና ሌሎችንም ሃብቶች ጠርጎ በመውሰድ ለዘመናት ሲፈስ ኖሯል። ከኢትዮጵያ እምብርት በመነሳት አገራትን አቆራርጦ የሚያልፈው፣ የዓለማችን ታላቁ ወንዝ አባይ በጋና ክረምት ሳይል በመፍሰስ የብዙዎች የህይወት ምንጭ ሆኖ አሁንም ፍሰቱን ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ልጅ የኢትዮጵያውያን አብሮነት ምሰሦ - የወንዞች ንጉሥ ታላቁ አባይ! አሁን ልጓም ተበጅቶለት በፍትሃዊነት ሁሉንም ለመጥቀም ተዘጋጅቶ የማይነጥፈው ጅረት ዘላለማዊ የመፍሰስ ሂደቱ እንደቀጠለ ነው። ኢትዮጵያውያን አመሉ ለከፋ፤ እሺ በጀ አልል ብሎ በእንቢታ ልቡን ባጸና ልጅ አብዝተው ያዝናሉ። የሀዘናቸው ጥግም በሕይወት ሳለ የሞተ ያክል በእንጉርጉሮ ሙሾ ያወርዱለታል። አባይም ይህ እጣ ፈንታ ገጥሞት "አመፀኛ ውሃ" ተብሎ በወቀሳ ተዚሞለታል። ለኢትዮጵያ ለዘመናት ሳይታዘዝ የኖረው አባይ የአዛዥ እጦት እንጂ በእምቢታ አልነበረም። በዚህ ውጣ በዚህ ግባ ባይ አጥቶ ቦዘነ። በዚህም ተራራውን እየሸሸ ቁልቁል እየተምዘገዘገ፣ ሲሻ እየጬሰ ቁልቁል ወርዶ ከዐለት ጋር እየተጋጨ መዳረሻውንና ማደሪያውን ይናፍቃል። በዚህም ቤቱን ረሳ። ወላጆቹን ትቶ ባእዳንን ብቻ ጦረ፣ ፊቱን በፍጹም ወደ ኋላ እንዳይመልስ እንደ ሎጥና ቤተሰቦቹ ተገዘተ። አባይ የባእዳንን ግዝት ከተፈጥሮ ጋር አስተባብሮ በመጠበቅ ሀገሩን ለቆ ከመውጣት ውጭ ቢደክመው የማረፍ፥ ቢመቸው የማልማት መብት ሊያገኝ አልቻለም። ይህ በኢትዮጵያ ልብ ውስጥ ቁጭት ፈጥሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ ለታላቅ ልጇ ማረፊያ ሠርታ ጎጆ ልታወጣ ቋመጠች። ፈተናው በዛ የፖለቲካ መልክ ይዞም አቅሟን ተፈታተነ። ስደተኛው አባይን ስላሳረፉት እርሱም ስለመገባቸው የግል ሀብት አድርገው የቆጠሩት የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጫና ፈጥረው የሀሳብ ጽንሱን ከታሪካዊና ቀጣናዊ ጠላቶች ጋር እየተባበሩ አቋረጡት። አባይን ገድቦ የመጠቀም የዘመናቱ የኢትዮጵያ መሪዎች ጉጉቱ ህልም ሆኖ ሐዘኑ ከነ ቁጭቱ ቀጠለ። እንጉርጉሮ ወቀሳ በበዛባቸው ስንኞች ቋጥሮ መዜሙን ቀጠለ። የኢትዮጵያ ዐይኖች ጀግንነት በአባይ ሲሸበብ ማየት አንገሸገሻቸው። የበይ ተመልካች መሆንና ከጓሯቸው ሞፈር አስቆርጦ መራብ አመማቸው። ኢትዮጵያዊነት ከዘመን ዘመን የማይነጥፍ፥ ልብ ለልብ የተሳሰረ ትውልድ ማንነት ማሳያ ሐውልት ነው። ትላንት ዛሬን እያቃና ነገን የሚገነባበት ሀገራዊ ራእይ ያላቸው መሪዎች ትስስር በአባይ ሲንጸባረቅ ይስተዋላል። ከ1929 እስከ 1950ቹ ያለው የአባይ ፖለቲካ ጉዳይ በብዙ ድርድሮችና ስምምነቶች ታጀበ። የጫና ፈተናው አየለና ገንብቶ የመጠቀም ጥንስስን ለቀጣይ ትውልድ እንዲሸጋገር አደረገ። ያኔ ነገን የተመለከተ ዐይን "ልጆቻችን ይሠሩታል" የሚል ቃል ሰጠና ኢትዮጵያ ልጆቿን በተስፋ ተጠባበቀች። ዘመን አለፈ ትውልድ ተተካ ልጆችም ተወለዱና የተስፋ ቀጠሮ ደረሰ ወርሃ መጋቢት 2003 ዓ/ም። በዚህ ቀን የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዜና በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ተበሰረ። ኢትዮጵያ እልል አለች፤ "እንጉርጉሮ ይብቃ" ተባለ በዜማ በዝማሬ አባይ ተሞገሰ። የአባይ የወቀሳ ጊዜ ተጠናቀቀ- የቁጭት ጊዜ አብቅቶ የስኬትና ማንሰራራት ጊዜ መጣ። ለግድቡ የ14 ዓመታት የግንባታ ሂደት ከአንድ ብር ጀምሮ አስተዋጽኦ ያደረጉ፣ በእውቀትና በጉልበት የተጉ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የደስታ ቀንም እውን ሆነ። በጉባ ሰማይ ስር አዲስ ክስተት፣ አዲስ ምዕራፍ፣ አዲስ ስም ተተከለ። አባይ ከሚል ነጠላ ስም ወደ "ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ" ተሻገረ። የድግቡ ሃይቅም "ንጋት" የሚል መጠሪያ ወጥቶለት ለኢትዮጵያ የንጋት ጸሃይ እየወጣች መሆኑን ለሁላችንም ብስራት ሆነ። "እንኳንም ጀመርን፣ እንኳንም በር ተከተፈተልን" እንጂ ያሉት ልበ ኩሩና ክንደ ብርቱ ኢትዮጵያውያን ጫናዎችን በአይበገሬነት መንፈስ ድባቅ እየመቱ ጉዞ ወደ ፊት ቀጠሉ። ወደ ተግባር ገብተው "ሕይወታችንንም ቢሆን ለአባይ አንሰስትም" አሉ። ግድቡን እንሠራለን ብለው የጀመሩት ኢትዮጵያውያን ናቸው። ከነ አባባላቸው "የነብር ጭራን አይያዙ፥ ከያዙም አይለቁ" ነውና ሥራውን ስለጀመሩት የአባይ ግድብ ጉዳይ ቀዳሚ አጀንዳቸውና ደም ስራቸው ሆኖ ቀጠለ። እንደ ዐይን ብሌናቸው ያዩ፣ ይጠብቁት እና ይሳሱለት ጀመር። የአልሸነፍ ባይነት ወኔን ከጀግንነት ጋር አጣምረው የያዙ ኢትዮጵያውያን የጠላት ነቀፋና ፕሮጀክቱን የማኮላሸት ሴራን እንደ ድር አብረው ተከላከሉ። የ"እንችላለን" ትርክትን በተግባር ነፍስ እየዘሩ እጅ ለእጅ ተያይዘው ጉዟቸውን ከሕዳሴ ጋር ቀጠሉ። በጉባ ምድር ላይ የአንድነታቸውን ቋሚ ሐውልትም ተከሉ። ኢትዮጵያውን ከአድዋ ጦርነት ወዲህ የአንድ ቃል ተናጋሪ የአንድ ልብ መካሪ ሆነው የተከሰቱበትና በአንድ የተመሙበት ትልቁ የታሪክ አሻራ አባይ በሕዳሴ ሆነ። የተማሪ ቦርሳ፣ የእናቶች መቀነት፣ የአረጋውያን የጡረታ ደብተር፣ የአርሶ አደሮች ጎተራ፣ የአርብቶ አደሮች በረት፣ የመንግሥት ሠራተኛው ፔሮል፣ የነጋዴው ኪስ እና የዳያስፖራ ዋሌት ሳይቀር በአባይ ላይ አሻራ አለው። የሕዳሴው ግድብ ውዝግብ ኢትዮጵያ ራሷን በዓለም መድረክ ከፍ አድርጋ ያሳየችበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የደረሰውን ውሃ አይሞላ ክስ በብስለት መክታ እውነትን ለዓለም ሕዝብ አስገንዝባለች። በዚህም የዓለም አቀፍ ሕግ አዋቂነቷንና አክባሪነቷን፣ የጋራ ተጠቃሚነት ፍላጎቷንና ለሰላም ያላትን አቋም ቁልጭ አድርጋ አረጋግጣለች። ድርድሮችን በድል የሚቋጩ ልጆቿ ደግሞ ኢትዮጵያውያን በሁሉም ዘርፍ ብቁ የመሆናቸው ነጸብራቅ ሆነው ተከሰቱ። ዘርፈ ብዙ የዲፕሎማሲ ሥራው ከማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ እስከ ጉምቱ አምባሳደሮች በተናበበ መልኩ ብቅ ብሎ አጀብ አስብሏል። ድርድሩ በመስመሩ፣ የዲፕሎማሲ ሥራው በሜዳው ፖለቲካ እና ሌላው የሀገር ጉዳይ በየፈርጁ እየቀጠለ የሕዳሴው ግድብም ለደቂቃ እንኳ ሳይቆም ይሠራ ነበር። ይህ የመብቃት፣ የማደግ፣ በጥበብ የመበልጸግ፣ በሀሳብና አቅም የመብሰል ሀገራዊ ማሳያ ነው። ለብዙ የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚሆን አሻጋሪ የተግባር ልምምድ መሆኑም አያሻማም። ለዚህ ግድብ ስኬት ደግሞ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን መሪ ሆነው ብቅ ያሉትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶር) ማንሳት ግድ ይላል። አዛዥ አጥቶ ቦዝኖ የነበረውን ጊዜ ለመካስ ና ብሎ የሚጣራውን አዛዥ "አቤት" ብሎ ትዕዛዝ ለመቀበል አባይ አላቅማማም። አሁን በሙሉ ልቡ ወደ ጫጉላ ቤቱ ገብቷል። የመስከረሙ ሙሽራ የቤት ሀብት ዘርፎ ለባዕድ አሳልፎ ከመስጠት ተቆጠበ። የበረሃው ሀሩር ሳይመታው በሀገሩ እፎይ ብሎ ብርሃንም ምግብም፣ ሀብትም ክብርም መሆን ጀመረና የኢትዮጵያን ክብር ዳግም ከፍ አደረገ። ሰው ተፈጥሮን ሲያዝ እሺ ይላል፥ ዝም ካሉት በራሱ ፍላጎት ይሔዳል። ይህ ተፈጥሯዊ የአባይ ግብር ተቀይሮ በሰዎች መታዘዝ ጀመረ። አፈርና ውሃ ማስቀረት ብቻ ሳይሆን ግዙፍ የብርሃን ምንጭ ሆኖ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ብርሃን መሆን ጀምሯል። በሕዳሴ ግድብ ታዞ ፊቱን ወደ ልማት ሥራ ያዞረው አባይ ያለፈውን ለመካስ ብዙ ጸጋዎችን ይዞ ተከሰቷል። የዓሳ ምርት፣ ግዙፍ ሀይቅ ከደሴቶች ጋር አንጣሎ በመያዝ የኢኮ ቱሪዝም ዘርፍ መሪ ሊሆን ቆርጦ ተነስቷል። አብሮ የመልማት የኢትዮጵያ ጽኑ ፍላጎት በወለደው እሳቤ ህዳሴ ግድብ የጎረቤት አገራት ሃብት ጭምር በመሆን ለማገልገል ተዘጋጅቷል። አባይ ሆይ ስምህ ከወቀሳ ወጥቶ በሙገሳ ስለተተካ እንኳን ደስ አለህ! እናቴ ሆይ የተፈታው መቀነትሽ ሀይል ስላመነጨ ለልጆችሽ ሀብት አውርሰሻልና ደስ ይበልሽ። ሀገሬ የብርሃን ዘመን ስለፈነጠቀብሽ እንኳን ደስ አለሽ! ሰላምና ፍቅር ለሁላችን ይሁን።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም