መነሻ - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ጫናን መቋቋም የሚችል ኢኮኖሚ ለመገንባት የታክስና ጉምሩክ ሕግ ተገዢነትን ማስፈን ይገባል - ገቢዎች ሚኒስቴር
Jun 10, 2023 26
ሀዋሳ ሰኔ 3/2015 (ኢዜአ)፡- ጠንካራና ጫናን መቋቋም የሚችል ሀገራዊ ኢኮኖሚ ለመገንባት የታክስና ጉምሩክ ሕግ ተገዢነትን ማረጋገጥ ከሁሉም ባለድርሻዎች የሚጠበቅ ኃላፊነት እንደሆነ የገቢዎች ሚኒስቴር ገለጸ። የደቡብ ክልል ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የዕውቅናና ሽልማት መርሀ ግብር የክልልና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በቡታጅራ ከተማ ተካሂዷል። በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የገቢዎች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ቱሉ የግብር ሥርዐቱን በማክበርና በማስከበር ጠንካራና ጫናን መቋቋም የሚችል ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ኢኮኖሚ መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል። በመሆኑም ጠንካራ የታክስ ሥርዐትን መገንባትና የታክስና ጉምሩክ ሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻዎች በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በሀገር ደረጃ ይህንን ለማሳካት የሚያስችል ከየካቲት 2015 ዓ.ም እስከ የካቲት 2016 ዓ.ም የሚቆይ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ተገዢነት ንቅናቄ "ግብር ለሀገር ክብር" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታውሰዋል። የደቡብ ክልል ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮችን ዕውቅናና ሽልማት የመስጠት መርሀግብርም የዚሁ ንቅናቄ አካል እንደሆነ ጠቅሰዋል። የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው ከውጭ እርዳታና የኢኮኖሚ ጫና ተላቀን ሀገራችንን በራሳችን አቅም ማሳደግና ማልማት የምንችለው የውስጥ ገቢያችን ላይ በትኩረት መሥራት ስንችል ነው ብለዋል። ለዚህም የተፈጥሮና የሰው ሀይል ፀጋዎችን ተጠቅሞ ኢኮኖሚን ማሳደግና ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት ተገቢውን ግብር በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ የተመዘገበውን የኢኮኖሚ ዕድገት በመጠቀም ገቢውን ማሳደግ እንደተቻለ ጠቅሰው፤ የክልሉ ገቢ ላለፉት አራት ዓመታት በአማካይ ከ30 በመቶ በላይ እያደገ መምጣቱን አስረድተዋል። በትኩረትና በታማኝነት መስራት ከተቻለ ከዚህ በላይ ወጪውን መሸፈንና የልማት ሥራዎችን በአግባቡ ለመስራት የሚያስችል ገቢ መሰብሰብ እንደሚቻል ጠቁመዋል። ግብር ከፋዩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን በማሳደግ የተሻለ ገቢ ማስገኘት እንዲችል ከመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች ጀምሮ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች በፍጥነት ወደ ሥራ ገብተው ገቢ ማመንጨት እንዲችሉ ማድረግና ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ከመንግስት አካላት የሚጠበቅ ተግባር እንደሆነ ገልፀዋል። ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር በታማኝነት መክፈላቸውን አጠናክረው በማስቀጠል በሀገራቸው ልማትና እድገት የበኩላቸውን አሻራ እንዲያኖሩ ጥሪ አቅርበዋል። ከተሸላሚ ግብር ከፋይች መካከል በዲላ ከተማ በዱቄት ፋብሪካ፣ በቡና ንግድና ሌሎች ሥራዎች የተሰማሩት አቶ የሱፍ ጠሀ 7 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ግብር በመክፈል ተሸላሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለ14 ዓመታት ያህል ግብር በታማኝነት በመክፈል ሲሸለሙ መቆየታቸውን ጠቅሰው፤ መሸለሜ በመንግስትና ህዝብ ዘንድ ከማገኘው ክብርና ፍቅር ባሻገር ለሀገሬ እድገት የሚጠበቅብኝን በማድረጌ ደስተኛ ያደርገኛል ብለዋል። ለሀገር የሚገባውን ግብር በታማኝነት መክፈል ጥቅሙ ለራስ እንደሆነም ተናግረዋል። በመርሀግብሩ ላይ 58 ለታክስ ህግ ተገዢና ታማኝ የሆኑ ግንባር ቀደም ግለሰብ ግብር ከፋዮች፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶች እና ሴክተር መስሪያ ቤቶች ዕውቅናና ሽልማት የተሰጣቸው ሲሆን ከ50 ሺህ 310 ብር እስከ 17 ሚሊዮን 914 ሺህ 763 ብር ድረስ ግብር የከፈሉ በደረጃ ሐ፣ ለ እና ሀ ግለሰብ ግብር ከፋዮች ተሸላሚ ሆነዋል።
የሰላም በሮች ለሁሉም ክፍት መደረጋቸው በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት ሆኗል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Jun 10, 2023 35
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፡- የሰላም በሮች ለሁሉም ኃይሎች ክፍት መደረጋቸው በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ፤ በተለያዩ ወቅታዊ አገራዊ ጉዳዩች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በአገሪቱ የሕግ የበላይነትን የማስፈንና ዘላቂ ሰላምን የማረጋገጥ እርምጃ የመንግሥት ቀዳሚ ተግባር ነው ብለዋል፡፡ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ግጭትና ጦርነት የዜጎችን ደኅንነትንና ነፃነት አደጋ ላይ የሚጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ሰላም በሌለበት ብልጽግና እንደማይረጋገጥ ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን የብልጽግና ተምሳሌት እንድትሆን እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሁን እየተረጋገጠ ያለውን አንጻራዊ ሰላም ቀጣይነቱን ማረጋገጥና ቀዳሚ ተግባር መሆን እንዳለበትም ጠቅሰዋል፡፡ የሰላም በሮችን ለሁሉም ኃይሎች ክፍት ማድረግ መቻሉ በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የሰሜኑ ግጭት በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ ስምምነት መሠረት በተቀመጠለት አቅጣጫ በስኬታማነት እየተፈጸም እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በጋምቤላ ክልሎች የሚገኙ ታጣቂዎችም በተከፈተው የሰላም በር መጠቀም በመቻላቸው የተረጋጉ እና ሰላም የሰፈነባቸው ክልሎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ከሸኔ ጋር የተጀመረው ሰላም የማስፈን ጥረትም ተጠናክሮ የሚቀጥል እንደሚሆንም ጠቁመዋል፡፡ የአማራ ክልል አሁን ላይ ሰላም መሆኑን ገልጸው፤ በኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ያሉትን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ በመደረጉ አብዛኞቹ መመለሳቸውን ገልጸዋል፡፡ አልፎ አልፎ ያፈነገጡትን ከአገር ሽማግሌዎች፣ ከኅብረተሰቡ እና ከራሳቸው ጋር በተደረገ ውይይት አብዛኞቹ ወደ ቀደመው ህይወታቸው እንዲመለሱ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ያልተመለሱት ላይ መንግሥት አስፈላጊ ያለውን ሕጋዊ እርምጃ መውሰዱን ጠቁመው፤ ይህ አሁንም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡ አሁን ላይ በአማራ ክልል በተደረገው ውይይት ሰላምና ጸጥታ እየሰፈነ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ዛሬም የኢትዮጵያን ሰላም የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ ኃይሎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ የተጀመረው ጠንካራ የሰላምና ደኅንነት ተቋም የመገንባት ሥራም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የተማርንበትን ትምህርት ቤት ለማዘመንና የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚደረገውን ጥረት ይበልጥ እናግዛለን- የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች
Jun 10, 2023 35
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፡- የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤትን ለማዘመንና የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ ለሚደረገው ጥረት ያላሰለሰ ድጋፍ እንደሚያደርጉ የቀድሞ ተማሪዎች ገለጹ። በ1917 ዓ.ም. እንደተመሰረተ የሚነገርለት ፋና ወጊው የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የአሁኑ ደግሞ የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንድ ክፍለ ዘመኑን ሊደፍን ሁለት ዓመታት ብቻ ቀርተውታል። ትምህርት ቤቱ ለአገሪቱ የሥልጣኔ ጉዞ ትልቅ ሚና ማበርከቱን በርካቶች ይናገሩለታል። የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪ አርቲስት ደበበ እሸቱ ትምህርት ቤቱ ለአገርና ለወገን የጠቀሙ በርካታ ምሁራንን አፍርቷል ብሏል። በየዘመኑ ከትምህርት ቤቱ የወጡ ሰዎች በተለያዩ ሙያ ዘርፎች ፈርጦች ሆነው አገራቸውን ማገልገላቸውን ገልፆ፤ ትምህርት ቤቱ እውቀትንና ክህሎትን ከማስጨበጥ ባለፈ ተማሪዎች በመልካም ሥነ-ምግባር ታንጸው እንዲወጡ በማድረግ ረገድ አስተዋጽዖ እንዳላቸው ተናግሯል። የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪዎች ማኅበር በማቋቋም ትምህርት ቤቱን በተለያዩ ዘርፎች እየደገፉ እንደሚገኙ ገልፆ፤ ይህም ለትምህርት ጥራት መምጣት የራሱ የሆነ አበርክቶ ይኖረዋል ነው ያለው። ሌላኛው የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪ ካፒቴን ከበደ ወልደፃዲቅ፤ ማኅበሩ ትምህርት ቤቱ የሚያስፈልጉትን አንዳንድ የትምህርት ቁሳቁስ መሣሪያዎችን ድጋፍ በማድረግ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል። በተለይም ለመማር ማስተማር አገልግሎቱ ጠቀሜታ ያላቸውን የኮምፒውተር ክፍሎች ከማደራጀት ባለፈ በማዕድ ማጋራትና ለተማሪዎች አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በማሟላት ለኮሌጁ እገዛ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ ጋረደው አጥናፍ እና ሰዓሊ ሉዑልሰገድ ረታ የተባሉ የቀደሞ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በበኩላቸው፤ ትምህርት ቤቱ በግብረገብነትና ሥነ-ምግባር አስተምህሮ ላሉበት ደረጃ ያበቃቸው በመሆኑ አሁን ያለው ተተኪ ትውልድ በተመሳሳይ ለስኬት እንዲበቃ ትምህርት ቤቱን መርዳትና መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። በመሆኑም እነርሱ በትምህርት ቤቱ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ትምህርት ለአንድ አገር እድገት ወሳኝ በመሆኑ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የተጀመረውን ሥራ ውጤታማ ለማድረግ የቀድሞ ተማሪዎች ያስተማራቸውን ትምህርት ቤት መርዳትና መደገፍ አለባቸው ሲል አርቲስት ደበበ እሸቱ ተናግሯል። ካፒቴን ከበደ በበኩላቸው፤ የቀድሞ ተማሪዎች ያስተማራቸውን ትምህርት ቤት ተመልሰው በመደገፍ የትምህርት ጥራት እንዲመጣ አስተዋጽዖ ማድረግ እንደሚገባቸው ነው የተናገሩት። አቶ ጋረደው አጥናፍ እና ሰዓሊ ሉዑልሰገድ ረታ በበኩላቸው፤ የአገር እድገት መሠረት የሆኑትን ትምህርት ቤቶች መደገፍ የውዴታ ግዴታ መሆኑን ጠቁመዋል። በመሆኑም የቀድሞ ተማሪዎች ያስተማራቸውን ትምህርት ቤት በመደገፍ የትምህርት ጥራት እንዲጠበቅ ያላሰለስ ድጋፍ ማድረግ አለባቸው ብለዋል። የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ተሾመ ፈይሳ በበኩላቸው፤ የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪዎች ለመማር ማስተማሩ ከሚያደርጉት እገዛ ባሻገር ለተማሪዎች ሞራል ግንባታ አዎንታዊ አስተዋጽዖ እያበረከቱ እንደሚገኙ አንስተዋል። በመሆኑም ይህን ጥሩ ተሞክሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች በማስፋት የቀድሞ ተማሪዎች የተማሩበትን ትምህርት ቤት እንዲደግፉ በማድረግ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት በሚደረገው ጥረት የራሳቸውን ጉልህ ሚና እንዲወጡ ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት።
የተጀመረው የፍትህ ተቋማት የለውጥ ፍኖታ ካርታ ትግበራ በትኩረት ሊሰራ ይገባል--አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jun 10, 2023 36
ጅግጅጋ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦ ፍትህ ለሰላም፣ ለዘላቂ ልማትና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዋሳኝ ሚና ስላለው የተጀመረው የፍትህ ተቋማት የለውጥ ፍኖታ ካርታ ትግበራ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። 3ኛው ሀገር አቀፍ የህግ አውጪዎች የጋራ የምክክር መድረክ በጅግጅጋ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንደተናገሩት መድረኩ በመንግስታት መካከል ያለውን ግንኙነት ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1231/2013 መሰረት በማድረግ በፌዴራል እና በክልሎች መካከል ያለ ግንኙነትን ለማጠናከር በየስድስት ወሩ የሚካሄድ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ፍትህ ለማረጋገጥና ለማጠናከር በፌዴራል የፍትህ ተቋማት የተጀመረው የፍትህ የለውጥ ፍኖታ ካርታ በየደረጃው ያሉ የፍትህ ተቋማት ለመተግበር መስራት ይገባቸዋል ብለዋል። "ፍትህ ለሰላም፣ ለዘላቂ ልማት፣ ለፖለቲካና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና አለው" ሲሉም አፈ-ጉባኤው ተናግረዋል። በህግ አውጪዎች መካከል የሚደረገው ውይይት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን፣ ዋስትና ያለው ዲሞክራሲ ለማረጋገጥ እና ፈጣን እድገት በማስመዝገብ፣ አንድ የፖለቲካ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመፍጠር ያግዛልም ብለዋል። የክልሎች እና የብሄረሰቦች ምክር ቤቶች እየተሳተፉበት በሚገኘው የምክክር መድረክም የእርስ በእርስ ግንኙነትን ከማጠናከር ባሻገር መልካም ተሞክሮዎች የሚለዋወጡበት እንደሆነም ጠቁመዋል። መድረኩ በፌዴራል ደረጃ በፍትህ ስርዓቱ ላይ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በክልሎችም ለማጠናከር የሚያግዝ ምክክር ይካሄድበታል ተብሏል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ፣ "እውነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት በየደረጃው የሚገኙ የፍትህ ተቋማት ተቋማዊ ነፃነታቸው ተጠብቆ በሰው ኃይል እና በቴክኖሎጂ ታግዘው መስራት ይጠበቅባቸዋል" ብለዋል። በሶማሌ ክልልም ከለውጡ በፊት የነበረ ሰፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስቀረት ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል፣ በዚህም ውጤቶች ታይተዋል ሲሉ ገልጸዋል። ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው መድረክ የፍትህ ተቋማት የለውጥ ፍኖታ ካርታ ስርዓት የጋራ ሰነድ እንዲሁም የፍርድ ቤቶች የአሰራር ለውጥ ላይ ያተኮረ ፍኖተ ካርታ ቀርቦ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል። በመድረኩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌደሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ቴዎድሮስ ምህረት፣ የፍትህ ሚኒስትር ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ እና የክልል፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር እና የተለያዩ ብሄረሰቦች ምክር ቤቶች አፈ-ጉባኤዎች እና ምክትል አፈ-ጉባኤዎች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ማዘመን የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ሥራዎች ተሰርተዋል - ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ
Jun 10, 2023 48
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ማዘመን የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ሥራዎች መሰራታቸውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ተናገሩ። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዘጋጅነት በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው "የሥራ ባህልን መለወጥና የዕይታ አድማስን ማስፋት" የውይይት መድረክ የተሳተፉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችና ሌሎች አካላት የአየር ኃይል የለውጥ ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ በተቋሙ የተወሰደው የለውጥ እርምጃ አገርን በችግር ውስጥም መገንባት እንደሚቻል ያሳየ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ አየር ኃይልም አስተማማኝ የሰው ኃይልና ዘመናዊ ትጥቅ እንዲኖር በማድረግ እንዲሁም ተቋሙ ፅዱና ማራኪ እንዲሆን ያስቻለ የተለያዩ የለውጥ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። የሰራዊቱን አቅም በመገንባት ተቋሙንም ከማንኛውም የፖለቲካ፣ የኃይማኖትና የብሔር አስተሳሰብ ነፃና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ኩራት እንዲሆን ማድረግ እንደተቻለም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ታላቅ አገር ናት ያሉት ሌተናል ጄነራል ይልማ፤ አገሪቷም ያላትን ታሪክ፣ የቆዳ ስፋትና የሕዝብ ብዛት ታሳቢ በማድረግ በአየር ኃይል ላይ በርካታ የለውጥ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል። በአየር ኃይል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊና የ5ኛ አየር ምድብ አዛዥ ኮሎኔል ብሩክ ሰይፉ፤ ባለፉት ሦስት ዓመታት የአጭር፣ የመካከለኛና የረዥም ጊዜ ዕቅድ በመንደፍ በተቋሙ ላይ ውጤታማ የልማት ሥራ ተሠርቷል ብለዋል። በዚህም በሰው ኃይልና በዘመናዊ ትጥቅ በማደራጀት የኢትዮጵያን አየር ክልል ማስጠበቅ የሚያስችል አስተማማኝ ተቋም መገንባት እንደተቻለ ገልጸዋል። የአየር ኃይልን ቅጥር ግቢ ውብና ማራኪ በማድረግ ምቹ የሥራ አካባቢን መፍጠር ያስቻለ ውጤታማ የልማት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በጉብኝቱ የተሳተፉ አካላትም አየር ኃይል ባጠረ ጊዜ በሰው ኃይል፣ በዘመናዊ ትጥቅ ግንባታ፣ ተቋም የማስዋብና የማልማት ሥራ ላይ ያከናወናቸው ተግባራት አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከጎብኝዎች መካከል አንዱ የሆኑት የዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ዋና ሥራ አስፈጻሚ መሐመድ ሐሰን በሰው ኃይልና ተቋማዊ የለውጥ ማሻሻያ በማድረግ የተሻለ ቁመና ላይ እንዲገኝ መደረጉ አስደናቂ ነው ብለዋል።
ፖለቲካ
የሰላም በሮች ለሁሉም ክፍት መደረጋቸው በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት ሆኗል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Jun 10, 2023 35
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፡- የሰላም በሮች ለሁሉም ኃይሎች ክፍት መደረጋቸው በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ፤ በተለያዩ ወቅታዊ አገራዊ ጉዳዩች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በአገሪቱ የሕግ የበላይነትን የማስፈንና ዘላቂ ሰላምን የማረጋገጥ እርምጃ የመንግሥት ቀዳሚ ተግባር ነው ብለዋል፡፡ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ግጭትና ጦርነት የዜጎችን ደኅንነትንና ነፃነት አደጋ ላይ የሚጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ሰላም በሌለበት ብልጽግና እንደማይረጋገጥ ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን የብልጽግና ተምሳሌት እንድትሆን እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሁን እየተረጋገጠ ያለውን አንጻራዊ ሰላም ቀጣይነቱን ማረጋገጥና ቀዳሚ ተግባር መሆን እንዳለበትም ጠቅሰዋል፡፡ የሰላም በሮችን ለሁሉም ኃይሎች ክፍት ማድረግ መቻሉ በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የሰሜኑ ግጭት በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ ስምምነት መሠረት በተቀመጠለት አቅጣጫ በስኬታማነት እየተፈጸም እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በጋምቤላ ክልሎች የሚገኙ ታጣቂዎችም በተከፈተው የሰላም በር መጠቀም በመቻላቸው የተረጋጉ እና ሰላም የሰፈነባቸው ክልሎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ከሸኔ ጋር የተጀመረው ሰላም የማስፈን ጥረትም ተጠናክሮ የሚቀጥል እንደሚሆንም ጠቁመዋል፡፡ የአማራ ክልል አሁን ላይ ሰላም መሆኑን ገልጸው፤ በኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ያሉትን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ በመደረጉ አብዛኞቹ መመለሳቸውን ገልጸዋል፡፡ አልፎ አልፎ ያፈነገጡትን ከአገር ሽማግሌዎች፣ ከኅብረተሰቡ እና ከራሳቸው ጋር በተደረገ ውይይት አብዛኞቹ ወደ ቀደመው ህይወታቸው እንዲመለሱ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ያልተመለሱት ላይ መንግሥት አስፈላጊ ያለውን ሕጋዊ እርምጃ መውሰዱን ጠቁመው፤ ይህ አሁንም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡ አሁን ላይ በአማራ ክልል በተደረገው ውይይት ሰላምና ጸጥታ እየሰፈነ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ዛሬም የኢትዮጵያን ሰላም የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ ኃይሎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ የተጀመረው ጠንካራ የሰላምና ደኅንነት ተቋም የመገንባት ሥራም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ማዘመን የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ሥራዎች ተሰርተዋል - ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ
Jun 10, 2023 48
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ማዘመን የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ሥራዎች መሰራታቸውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ተናገሩ። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዘጋጅነት በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው "የሥራ ባህልን መለወጥና የዕይታ አድማስን ማስፋት" የውይይት መድረክ የተሳተፉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችና ሌሎች አካላት የአየር ኃይል የለውጥ ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ በተቋሙ የተወሰደው የለውጥ እርምጃ አገርን በችግር ውስጥም መገንባት እንደሚቻል ያሳየ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ አየር ኃይልም አስተማማኝ የሰው ኃይልና ዘመናዊ ትጥቅ እንዲኖር በማድረግ እንዲሁም ተቋሙ ፅዱና ማራኪ እንዲሆን ያስቻለ የተለያዩ የለውጥ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። የሰራዊቱን አቅም በመገንባት ተቋሙንም ከማንኛውም የፖለቲካ፣ የኃይማኖትና የብሔር አስተሳሰብ ነፃና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ኩራት እንዲሆን ማድረግ እንደተቻለም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ታላቅ አገር ናት ያሉት ሌተናል ጄነራል ይልማ፤ አገሪቷም ያላትን ታሪክ፣ የቆዳ ስፋትና የሕዝብ ብዛት ታሳቢ በማድረግ በአየር ኃይል ላይ በርካታ የለውጥ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል። በአየር ኃይል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊና የ5ኛ አየር ምድብ አዛዥ ኮሎኔል ብሩክ ሰይፉ፤ ባለፉት ሦስት ዓመታት የአጭር፣ የመካከለኛና የረዥም ጊዜ ዕቅድ በመንደፍ በተቋሙ ላይ ውጤታማ የልማት ሥራ ተሠርቷል ብለዋል። በዚህም በሰው ኃይልና በዘመናዊ ትጥቅ በማደራጀት የኢትዮጵያን አየር ክልል ማስጠበቅ የሚያስችል አስተማማኝ ተቋም መገንባት እንደተቻለ ገልጸዋል። የአየር ኃይልን ቅጥር ግቢ ውብና ማራኪ በማድረግ ምቹ የሥራ አካባቢን መፍጠር ያስቻለ ውጤታማ የልማት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በጉብኝቱ የተሳተፉ አካላትም አየር ኃይል ባጠረ ጊዜ በሰው ኃይል፣ በዘመናዊ ትጥቅ ግንባታ፣ ተቋም የማስዋብና የማልማት ሥራ ላይ ያከናወናቸው ተግባራት አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከጎብኝዎች መካከል አንዱ የሆኑት የዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ዋና ሥራ አስፈጻሚ መሐመድ ሐሰን በሰው ኃይልና ተቋማዊ የለውጥ ማሻሻያ በማድረግ የተሻለ ቁመና ላይ እንዲገኝ መደረጉ አስደናቂ ነው ብለዋል።
መደበኛ ፖሊስን የተቀላቀሉ የቀድሞ ልዩ ሃይል አባላት ለፖሊስ አቅም መጠናከር የበኩላቸውን ሚና መጫወት አለባቸው - አቶ ደሳለኝ ጣሰው
Jun 10, 2023 33
ባህርዳር ሰኔ 03/2015(ኢዜአ)፦ መደበኛ ፖሊስን የተቀላቀሉ የቀድሞ ልዩ ሃይል አባላት ልምዳቸውንና እውቀታቸውን በመጠቀም ለፖሊስ አቅም መጠናከር የበኩላቸውን ሚና መጫወት እንዳለባቸው የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ገለጹ። የክልሉ የቀድሞ ልዩ ሃይል አባላትን በተለያዩ የጸጥታ ዘርፎች መልሶ ለማደራጀት በተወሰደው እርምጃ የመደበኛ ፖሊስን የመረጡትን "ወንጀልን የመከላከል የመደበኛ ፖሊስ" ስልጠና በመውሰድ በዛሬው እለት ተመርቀዋል። የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንዳስታወሱት፤ በክልሎች የሚገኙ የልዩ ሃይል አባላትን ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች ማካተት ያስፈለገው ጠንካራ አገራዊ የጸጥታ መዋቅር ለመገንባት ነው። የቀድሞ የአማራ ልዩ ሃይል አባላትንም እንደየ ምርጫቸው በመደበኛ፣ በማረሚያ ቤት፣ በአድማ ብተናና በፌደራል ፖሊስ እንዲሁም በመከላከያ ሰራዊት በማካተት የማደራጀት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የህዝቡን ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ወጥነት ያለውና ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር መገንባት በማስፈለጉ መሆኑን አስረድተዋል። ጠንካራ የጸጥታ አካል እንዳይኖር የሚፈልጉ ሃይሎች የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በማናፈስና ውዥንብር በመፍጠር ልዩ ሃይሉን ለመበተን ያሴሩት ሴራ ከሽፏል ብለዋል። የወንጀል መከላከል ስልጠና ወስደው የመደበኛ ፖሊስን የተቀላቀሉ የቀድሞ ልዩ ሃይል አባላትም ልምዳቸውንና እውቀታቸውን በመጠቀም ለክልሉ ፖሊስ አቅም መጠናከር የበኩላቸውን ሚና መጫወት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደጀኔ ልመንህ በበኩላቸው ስልጠና የወሰዱ የዛሬ ተመራቂዎች የሚሰጣቸውን ፖሊሳዊ ተልእኮ በመወጣት ህዝባዊ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የቀድሞ የአማራ ልዩ ሀይል አባላት ፖሊስን መቀላቀላቸው ለክልሉ መደበኛ ፖሊስ ትልቅ አቅም ነው ብለዋል። አባላቱ በስልጠናው ያገኙትን ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት በመጠቀም ሰላምን በማስፈንና መረጋጋትን በመፍጠር ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የክልሉን ሰላም የማይፈልጉ ሃይሎች የሚያሰራጩትን የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ወደ ጎን በመተው ፖሊሳዊ ሃላፊነታቸውን በአግባቡ ለመወጣት መዘጋጀት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ የክልሉ የጸጥታ መዋቅር ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልልና የዞን አካላት መሳተፋቸው ታውቋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከራሱ በፊት ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መቆም ቀዳሚውና ዋነኛው እሴቱ ነው--መከላከያ ሚኒስቴር
Jun 10, 2023 56
አዲስ አበባ ሰኔ 03/2015(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ቁልፍ እሴት ከሆኑት ቀዳሚውና ዋናው ከራስ በፊት ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መቆም መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ዩኤስኤአይዲ (USAID) ሰሞኑን አጣርቻለሁ ብሎ ባወጣው መግለጫ ለሰብአዊ እርዳታ የመጣን እህል ከሌሎች መንግስታዊ አካላት ጋር በመሆን መከላከያ ሰራዊታችንም እንደተጠቀመ አድርጎ ያቀረበውን ሪፖርት የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ሲዘግቡት አስተውለናል ብሏል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራና ዘመናዊ መሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ ሰብዓዊ ድጋፍ የሚደረግላቸውን ወገኖቹን ቀለብ ሊቀማ ቀርቶ፤ ከቀለቡ ቀንሶ የሚያካፍል ሰራዊት መሆኑን የሃገሩ ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ በአጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሰላም ማስከበር በተሰማራባቸው ቦታዎች ሁሉ የተመሰከረለት መሆኑን ገልጿል። ኢትዮጵያ ለሰራዊቷ ደመወዝና ቀለብ መስጠት በመጀመር ቀዳሚ ነን ከሚሉ ሃገራት ተርታ የምትሰለፍ ነፃ እና ታሪካዊት ሃገር መሆኗን በመግለጫው የጠቀሰው የመከላከያ ሚኒስቴር የሰራዊቱ ቀለብ ለሃገር ውስጥ ነጋዴዎች እድሉን በመስጠት በግልፅ ጨረታ ተወዳድረው ስንዴም ሆነ ሌሎች ምግብ ነክ ፍጆታዎች የሚቀርብለት በተሟላ አሰራር የሚመራ ሰራዊት ነው ብሏል። ዩኤስኤአይዲ በሠጠው መግለጫ መሠረት ምናልባት የመከላከያ አባል የሆነ ወታደር በማይመለከተው ገብቶ ከመዋቅር ውጪ ሕግ የማስከበር ሥራውን ተጠቅሞ ከሌቦች ጋር በመተባበር እርዳታ ተሰርቆ እንዲወጣ በግል የተባበረ ካለ እና ተጣርቶ ከተገኘ የአገር መከላከያ ሠራዊት አመራር የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቋል። መከላከያ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦ ከኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር የተሰጠ መግለጫ ሰኔ 03/2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ቁልፍ እሴት ከሆኑት ቀዳሚውና ዋናው ከራስ በፊት ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መቆም ነው፡፡ ዩኤስኤአይዲ (USAID) ሰሞኑን አጣርቻለሁ ብሎ ባወጣው መግለጫ ለሰብአዊ እርዳታ የመጣን እህል ከሌሎች መንግስታዊ አካላት ጋር በመሆን መከላከያ ሰራዊታችንም እንደተጠቀመ አድርጎ ያቀረበውን ሪፖርት የተለያዩ ሚዲያዎች ሲዘግቡት አስተውለናል፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራ ዘመናዊ ሰራዊት ነው፡፡ ሰብዓዊ ድጋፍ የሚደረግላቸውን ወገኖቹን ቀለብ ሊቀማ ቀርቶ፤ ከቀለቡ ቀንሶ የሚያካፍል ሰራዊት መሆኑን የሃገሩ ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ በአጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሰላም ማስከበር በተሰማራባቸው ቦታዎች ሁሉ የዕለት ከዕለት ተግባሩ መሆኑን የደረሰላቸው ህዝቦች፤ መንግስታት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሁሉ የሚያውቁት ሰመ ጥር ህዝባዊ ሰራዊት ነው፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ ለሰራዊቷ ደመወዝና ቀለብ መስጠት ከጀመረች፤ ቀዳሚ ነን ከሚሉ ሃገራት ተርታ የምትሰለፍ ነፃ እና ታሪካዊት ሃገር ናት፡፡ ሰራዊታችን ዘመናዊ ነው ከሚያስብሉት አንዱ ደግሞ ይኸው ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው የሎጂስቲክ ግዥ እና አቅርቦት ጉዳይ ነው፡፡ የሰራዊታችን ቀለብ ለሃገር ውስጥ ነጋዴዎች እድሉን በመስጠት በግልፅ ጨረታ ተወዳድረው ስንዴም ሆነ ሌሎች ምግብ ነክ ፍጆታዎች የሚቀርብለት በተሟላ አሰራር እና አመራር የሚመራ ሰራዊት ነው፡፡ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት፡- 1ኛ/ ሠራዊታችን በቂ ሎጄስቲክ ያለው በዓለም አቀፍና በአገር ውስጥ ለተፈናቀሉትና በድርቅ ለተጎዱት በዓይነትና በገንዘብ የሚረዳ እንጂ ተቸግሮ ከአሰራር ውጭ የሚጠቀም አይደለም። 2ኛ/ ሠራዊታችን ማንኛውንም ዓይነት ምግብ በበጀቱ በሕግና በግልፅ ጨረታ ገዝቶ የሚጠቀም እንጂ ተቸግሮ የሕዝብ እርዳታ አካባቢ ሄዶ እርዳታ ላይ የሚሻኮትበት ዓይነት ድህነት የለበትም። ጥቆማ የሰጠ አካል እንኳ ቢኖር እስኪጣራ ሳይጠበቅ፤ እንደ ተቋምና እንደ ሠራዊት ስም የሚያጠፋ የሚዲያ ሽፋን መስጠት የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት ክብር ይነካል። 3ኛ/ ምንም እንኳን አገራችን በሚሊዮን የሚቆጠር እርዳታ ጠባቂ ሕዝብ ቢኖራትም ሠራዊቷን መመገብ የምትችልና በቂ ምግብና በጄት በመመደብ ሠራዊቱ ራሱ በሕግና በተቋም ሎጂስትክ አማካኝነት የምትመግብ አገር ናት። ሠራዊታችንም ኩሩና የችግረኞችን ስንዴ የማይሻማ ፕሮፌሽናል ሠራዊት ነው። ስለሆነም የእርዳታ ስንዴ የሚጠቀም ተቋም ወይም ዩኒት ወይም ወታደር የለንም። 4ኛ/ ዩኤስኤአይዲ (USAID) በሠጠው መግለጫ መሠረት ምናልባት የመከላከያ አባል የሆነ ወታደር በማይመለከተው ገብቶ ከመዋቅር ውጪ ሕግ የማስከበር ሥራውን ተጠቅሞ ከሌቦች ጋር በመተባበር እርዳታ ተሰርቆ እንዲወጣ በግል የተባበረ ካለ እና ተጣርቶ ከተገኘ የአገር መከላከያ ሠራዊት አመራር የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል። መከላከያ ሰራዊት ለሃገሩም ሆነ ለዓለም አቀፍ ሰላም መከበር መሰዋትነት የሚከፍል ምስጉን ሰራዊት ሆኖ እያለ፤ በአገራችን ውስጥና በውጪ አገር ያሉ ጥቂት የአገር መከላከያ ሠራዊት ጥላቻ ያላችው ፅንፈኞች እንዳሉ እናውቃለን። መካላከያን የማጠልሸት ሥራ የቆየና የለመድነው ነው። የመከላከያ ሠራዊታችንን ህዝባዊ ተፈጥሮ፣ አሰራርና ሥርዓት ሳይታወቅና መረጃ እንኳ ቢመጣ፤ አጣርቶ ሳይታወቅ፤ መረጃ የቀረበበት አካል ሳይጠየቅ፤ የሚዲያ ሽፋን መሰጠት ትክክል አይደለም ብለን እናምናለን። የሚመለከታቸው የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶችና የኢትዮጵያ መንግሥት እንዲያጣሩ እንተባበራለን። ከተጣራ በኋላ ሁሉንም ለሕዝብ ይፋ እናደርጋለን። የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር
የሀገር አቀፍ ሕግ አውጪዎች የጋራ የምክክር መድረክ በጅግጅጋ ይካሄዳል
Jun 9, 2023 95
ጅግጅጋ ሰኔ 2/2015(ኢዜአ)፦ የሀገር አቀፍ ሕግ አውጪዎች የጋራ የምክክር መድረክ ነገ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እንደሚካሄድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉበዔ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ፣በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ፣ የፍትሕ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ፣ የፌዴራል፣ የክልል እና የሁለቱ ከተማ መስተዳደር ምክር ቤቶች አፈ-ጉባዔዎች ማምሻውን ጅግጅጋ ከተማ ገብተዋል። የሕግ አውጪዎቹ ጅግጅጋ ሲደርሱ በሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ዑመር እና በክልሉ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ የሚካሄደው መድረክ በፌዴራል እና በክልል መንግሥታት፣ እንዲሁም በክልሎች መንግስታት መካከል ያለው ግንኙነት ጥንካሬዎች ለማስቀጠል እና የሚያጋጥሙ ክፍተቶችን ለመሙላት ያለመ ነው። በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን፣ ዋስትና ያለው የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለማረጋገጥ፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ልማትን ለማስቀጠል የመድረኩ ፋይዳ የጎላ እንደሚሆን በሕዝብ ተወካዮች ምከር ቤት የሚዲያ ዘርፍ ዳይሬክተር ወይዘሮ ብስራት ሽፈራው ገልጸዋል።
የሩሲያና የኢትዮጵያ አጋርነትን በተለያዩ የትብብር መስኮች ለማጠናከር እየተሰራ ነው - አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን
Jun 9, 2023 69
አዲስ አበባ ሰኔ 2/2015(ኢዜአ):- ለረጅም ዓመታት የዘለቀውን የኢትዮጵያና የሩሲያ ወዳጅነት በተለያዩ የትብብር መስኮች ይበልጥ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን ተናገሩ። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን ለኢዜአ እንደገለጹት ሁለቱ አገራት ለበርካታ ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት አላቸው። የኢትዮ-ሩሲያ የመንግሥትና የሕዝብ ለሕዝብ ወዳጅነት የጋራ ጥቅምን እንዲሁም መተማመንን መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። እያደገ የመጣውን የሁለቱ አገራት አጋርነት በኢኮኖሚ የትብብር መስክ ይበልጥ ሊያዳብሩ የሚችሉባቸው ዕድሎች መኖሩንም ነው የገለጹት። ይህንንም ተከትሎ አገራቱን በምጣኔ ኃብት መስክ ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ሰላም ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና መረጋጋት ትልቅ ትሩፉት እንዳለው ጠቁመው የኢትዮጵያ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም በሰላም ግንባታና በሌሎች ተያያዥ ሥራዎች ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸዋል። አገራቱ የሁለትዮሽ ብቻ ሳይሆን በባለብዙ ወገን መድረኮችም ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቁመው ይህንን ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል ነው ያሉት። በሌላ በኩል ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ጋር ያላትን አጋርነት ለማጠናከር እንደምትሰራ ገልጸዋል። በተለይም በአፍሪካ ኅብረት ትኩረት የተሰጠው 'ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ' መርህ እውን እንዲሆን አገራቸው ጽኑ እምነት አላት ብለዋል። ኢትዮጵያና ሩሲያ ከ125 ዓመታት በላይ ወዳጅነት ያላቸው አገራት ናቸው።
ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማሻገር የአሁኑ ትውልድ በዘመኑ ጠንክሮ መስራት እንዳለበት ተመለከተ
Jun 9, 2023 72
ሰኔ 02/2015 (ኢዜአ) ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች አገር ለማሻገር የአሁኑ ትውልድ በዘመኑ ያሉትን ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎችን በበጎ ተጠቅሞ ጠንክሮ መስራት እንዳለበት ተመለከተ። 32ኛው የጉሚ በለል የውይይት መድረክ "ቃል እና ተግባር፡ ከትውልድ እስከ ትውልድ” በሚል መሪ ሃሳብ በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ተካሄዷል፡፡ በውይይቱ ላይ የተገኙት የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሃይሉ አዱኛ ፤ የአንድን ትውልድ ማንነትና ምንነት የሚወስኑት ትውልዱ በዘመኑ ያሉ ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎችን ለመሻገር የሚያደርጋቸው ጥረቶች ናቸው" ብለዋል። "ሀገር በትውልድ ቅብብሎሽ ይገነባል" ያሉት አቶ ሃይሉ፤ ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ሀገር ማሻገር የሚቻለው የአሁኑ ትውልድ በዘመኑ ያሉትን አማራጮች ተጠቅሞ ጠንክሮ ሲሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የመድረኩ መሪ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ብርሃኑ ሌንጂሶ በበኩላቸው በትልቁ የሚገነባው ማህበራዊ እሴት መነሻው ሰው ለራሱ ከሚገባው ቃል ኪዳን ነው ብለዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ትውልድም በቃሉ ላይ የተመሰረተ የሀገር ግንባታ እንደሚያካሄድ ተናግረዋል። በመድረኩ የመነሻ የውይይት ጽሁፍ ያቀረቡት በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ዮሴፍ ቤኮ የተገባው ቃል በድርጊት የማይገለጽ ከሆነ እንደባከነ ይቆጠራል ብለዋል። ቃል እና ተግባር እንደ ሰንሰለት የተሳሰረ ያሉ ሲሆን ትውልድም ካለፈው ከአሁኑና ከሚመጣው ጋር የተሳሰረ ነው ብለዋል። በዚህም የመደመር ትውልድም ካለፈው የተገኘውን በጎ ውጤት እንደ ስንቅ በመያዝ ለሚመጣው ትውልድ ቃሉን ወደ ተሻለ ድርጊት መቀየር እንዳለበት በመግለጽ። በውይይቱ ላይ ተሳታፊ ከነበሩት ተማሪዎች መካከል ከአምቦ ኢፈ ቦሩ 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምርት ቤት የመጣችው የ9ኛ ክፍልተማሪ ፅዮን ሁምኔሳ በሰጠችው አስተያየት፤ "እኛ የመደመር ትውልድ የቃል ብቻ ሳንሆን የተግባር ትውልድ መሆናችንንም ጠንክረን በመስራት እናስመሰክራለን ብላለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በመደመር ትውልድ መጽሓፋቸው አንድ ትውልድ በዘመኑ ያሉ ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎችን ለመሻገር የሚያደርጋቸው ጥረቶች ከግምት በማስገባት ስለ ትውልዱ ያሰፈሩት ሀሳብ በመድረኩ ተወስቷል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር መጻሕፍት ኢትዮጵያን ለማስቀጠል መሰረት የሚጥሉ እሳቤዎችን የያዙ ናቸው - አርቲስት ደበበ እሸቱ
Jun 9, 2023 265
አዲስ አበባ ሰኔ 2/2015(ኢዜአ)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሶስቱ የመደመር መጻሕፍት ኢትዮጵያን ለማስቀጠል መሰረት የሚጥሉ እሳቤዎችን የያዙ መሆናቸውን አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ገለጹ። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዘጋጅነት "የመደመር ጉዞ" በሚል መሪ ሀሳብ በቢሾፍቱ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። በውይይቱም የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች አካላት ተሳትፈዋል። የመደመር እሳቤ ይዟቸው የመጡ መልካም አጋጣሚዎች፣ በሂደቱ እያጋጠሙ የሚገኙ ተግዳሮቶችና መፍትሔ አመላካች ጉዳዮችን የሚዳስሱ የማጠንጠኛ ሀሳቦች ላይ ምክክር ተደርጓል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የመደመርን ፋይዳ የሚያመላክቱ እሳቤዎችን ያካተቱ ሶስት መጻህፍት ለንባብ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። የስራ ባህልን ለማጎልበት እና በስራ ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን መፍትሔ ለመስጠት አመላካች ሀሳቦችን መካፈል የውይይቱ ዓላማ መሆኑን አመልክተዋል። የመደመር እሳቤ የሚቆም ሳይሆን ቀጣይነት ያለው ሂደት እንደሆነም ተናግረዋል። የመድረኩ ተሳታፊ አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ያለፈውን ዘመንና የአሁኑን ትውልድ ጉዞ እና ተሞክሮ አቅርበዋል። ጭፍን ጥላቻ እና ትችትን በማስወገድ የተሰነዱ መጻሕፍት አንብቦ በሚገባ አሰናስሎ መገንዘብ እና መረዳት ያስፈልጋል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሶስቱ የመደመር እሳቤ መጻሕፍት ቀጣይ የኢትዮጵያን እጣ ፋንታ ለመወሰን መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በውይይቱም የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የስራ ባህልን በማሻሻል ውጤታማ የልማት ምህዳርን መፍጠር እንደሚገባ ተገልጿል። እያንዳንዱ ዜጋ በስራ ሂደት የተሻለ ትጋት እና ተነሳሽነትን በመላበስ ኢትዮጵያ ያላትን ጸጋ አልምቶ በመጠቀም እድገትና ብልጽግናዋን ማስቀጠል እንደሚያስፈልግም ተጠቁሟል።
ፖለቲካ
የሰላም በሮች ለሁሉም ክፍት መደረጋቸው በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት ሆኗል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Jun 10, 2023 35
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፡- የሰላም በሮች ለሁሉም ኃይሎች ክፍት መደረጋቸው በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ፤ በተለያዩ ወቅታዊ አገራዊ ጉዳዩች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በአገሪቱ የሕግ የበላይነትን የማስፈንና ዘላቂ ሰላምን የማረጋገጥ እርምጃ የመንግሥት ቀዳሚ ተግባር ነው ብለዋል፡፡ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ግጭትና ጦርነት የዜጎችን ደኅንነትንና ነፃነት አደጋ ላይ የሚጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ሰላም በሌለበት ብልጽግና እንደማይረጋገጥ ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን የብልጽግና ተምሳሌት እንድትሆን እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሁን እየተረጋገጠ ያለውን አንጻራዊ ሰላም ቀጣይነቱን ማረጋገጥና ቀዳሚ ተግባር መሆን እንዳለበትም ጠቅሰዋል፡፡ የሰላም በሮችን ለሁሉም ኃይሎች ክፍት ማድረግ መቻሉ በመላ አገሪቱ እየሰፈነ ላለው አንጻራዊ ሰላም መሠረት መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የሰሜኑ ግጭት በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ ስምምነት መሠረት በተቀመጠለት አቅጣጫ በስኬታማነት እየተፈጸም እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በጋምቤላ ክልሎች የሚገኙ ታጣቂዎችም በተከፈተው የሰላም በር መጠቀም በመቻላቸው የተረጋጉ እና ሰላም የሰፈነባቸው ክልሎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ከሸኔ ጋር የተጀመረው ሰላም የማስፈን ጥረትም ተጠናክሮ የሚቀጥል እንደሚሆንም ጠቁመዋል፡፡ የአማራ ክልል አሁን ላይ ሰላም መሆኑን ገልጸው፤ በኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ያሉትን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ በመደረጉ አብዛኞቹ መመለሳቸውን ገልጸዋል፡፡ አልፎ አልፎ ያፈነገጡትን ከአገር ሽማግሌዎች፣ ከኅብረተሰቡ እና ከራሳቸው ጋር በተደረገ ውይይት አብዛኞቹ ወደ ቀደመው ህይወታቸው እንዲመለሱ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ያልተመለሱት ላይ መንግሥት አስፈላጊ ያለውን ሕጋዊ እርምጃ መውሰዱን ጠቁመው፤ ይህ አሁንም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡ አሁን ላይ በአማራ ክልል በተደረገው ውይይት ሰላምና ጸጥታ እየሰፈነ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ዛሬም የኢትዮጵያን ሰላም የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ ኃይሎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ የተጀመረው ጠንካራ የሰላምና ደኅንነት ተቋም የመገንባት ሥራም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ማዘመን የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ሥራዎች ተሰርተዋል - ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ
Jun 10, 2023 48
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ማዘመን የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ሥራዎች መሰራታቸውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ተናገሩ። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዘጋጅነት በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው "የሥራ ባህልን መለወጥና የዕይታ አድማስን ማስፋት" የውይይት መድረክ የተሳተፉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችና ሌሎች አካላት የአየር ኃይል የለውጥ ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ በተቋሙ የተወሰደው የለውጥ እርምጃ አገርን በችግር ውስጥም መገንባት እንደሚቻል ያሳየ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ አየር ኃይልም አስተማማኝ የሰው ኃይልና ዘመናዊ ትጥቅ እንዲኖር በማድረግ እንዲሁም ተቋሙ ፅዱና ማራኪ እንዲሆን ያስቻለ የተለያዩ የለውጥ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። የሰራዊቱን አቅም በመገንባት ተቋሙንም ከማንኛውም የፖለቲካ፣ የኃይማኖትና የብሔር አስተሳሰብ ነፃና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ኩራት እንዲሆን ማድረግ እንደተቻለም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ታላቅ አገር ናት ያሉት ሌተናል ጄነራል ይልማ፤ አገሪቷም ያላትን ታሪክ፣ የቆዳ ስፋትና የሕዝብ ብዛት ታሳቢ በማድረግ በአየር ኃይል ላይ በርካታ የለውጥ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል። በአየር ኃይል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊና የ5ኛ አየር ምድብ አዛዥ ኮሎኔል ብሩክ ሰይፉ፤ ባለፉት ሦስት ዓመታት የአጭር፣ የመካከለኛና የረዥም ጊዜ ዕቅድ በመንደፍ በተቋሙ ላይ ውጤታማ የልማት ሥራ ተሠርቷል ብለዋል። በዚህም በሰው ኃይልና በዘመናዊ ትጥቅ በማደራጀት የኢትዮጵያን አየር ክልል ማስጠበቅ የሚያስችል አስተማማኝ ተቋም መገንባት እንደተቻለ ገልጸዋል። የአየር ኃይልን ቅጥር ግቢ ውብና ማራኪ በማድረግ ምቹ የሥራ አካባቢን መፍጠር ያስቻለ ውጤታማ የልማት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በጉብኝቱ የተሳተፉ አካላትም አየር ኃይል ባጠረ ጊዜ በሰው ኃይል፣ በዘመናዊ ትጥቅ ግንባታ፣ ተቋም የማስዋብና የማልማት ሥራ ላይ ያከናወናቸው ተግባራት አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከጎብኝዎች መካከል አንዱ የሆኑት የዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ዋና ሥራ አስፈጻሚ መሐመድ ሐሰን በሰው ኃይልና ተቋማዊ የለውጥ ማሻሻያ በማድረግ የተሻለ ቁመና ላይ እንዲገኝ መደረጉ አስደናቂ ነው ብለዋል።
መደበኛ ፖሊስን የተቀላቀሉ የቀድሞ ልዩ ሃይል አባላት ለፖሊስ አቅም መጠናከር የበኩላቸውን ሚና መጫወት አለባቸው - አቶ ደሳለኝ ጣሰው
Jun 10, 2023 33
ባህርዳር ሰኔ 03/2015(ኢዜአ)፦ መደበኛ ፖሊስን የተቀላቀሉ የቀድሞ ልዩ ሃይል አባላት ልምዳቸውንና እውቀታቸውን በመጠቀም ለፖሊስ አቅም መጠናከር የበኩላቸውን ሚና መጫወት እንዳለባቸው የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ገለጹ። የክልሉ የቀድሞ ልዩ ሃይል አባላትን በተለያዩ የጸጥታ ዘርፎች መልሶ ለማደራጀት በተወሰደው እርምጃ የመደበኛ ፖሊስን የመረጡትን "ወንጀልን የመከላከል የመደበኛ ፖሊስ" ስልጠና በመውሰድ በዛሬው እለት ተመርቀዋል። የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንዳስታወሱት፤ በክልሎች የሚገኙ የልዩ ሃይል አባላትን ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች ማካተት ያስፈለገው ጠንካራ አገራዊ የጸጥታ መዋቅር ለመገንባት ነው። የቀድሞ የአማራ ልዩ ሃይል አባላትንም እንደየ ምርጫቸው በመደበኛ፣ በማረሚያ ቤት፣ በአድማ ብተናና በፌደራል ፖሊስ እንዲሁም በመከላከያ ሰራዊት በማካተት የማደራጀት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የህዝቡን ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ወጥነት ያለውና ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር መገንባት በማስፈለጉ መሆኑን አስረድተዋል። ጠንካራ የጸጥታ አካል እንዳይኖር የሚፈልጉ ሃይሎች የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በማናፈስና ውዥንብር በመፍጠር ልዩ ሃይሉን ለመበተን ያሴሩት ሴራ ከሽፏል ብለዋል። የወንጀል መከላከል ስልጠና ወስደው የመደበኛ ፖሊስን የተቀላቀሉ የቀድሞ ልዩ ሃይል አባላትም ልምዳቸውንና እውቀታቸውን በመጠቀም ለክልሉ ፖሊስ አቅም መጠናከር የበኩላቸውን ሚና መጫወት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደጀኔ ልመንህ በበኩላቸው ስልጠና የወሰዱ የዛሬ ተመራቂዎች የሚሰጣቸውን ፖሊሳዊ ተልእኮ በመወጣት ህዝባዊ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የቀድሞ የአማራ ልዩ ሀይል አባላት ፖሊስን መቀላቀላቸው ለክልሉ መደበኛ ፖሊስ ትልቅ አቅም ነው ብለዋል። አባላቱ በስልጠናው ያገኙትን ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት በመጠቀም ሰላምን በማስፈንና መረጋጋትን በመፍጠር ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የክልሉን ሰላም የማይፈልጉ ሃይሎች የሚያሰራጩትን የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ወደ ጎን በመተው ፖሊሳዊ ሃላፊነታቸውን በአግባቡ ለመወጣት መዘጋጀት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ የክልሉ የጸጥታ መዋቅር ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልልና የዞን አካላት መሳተፋቸው ታውቋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከራሱ በፊት ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መቆም ቀዳሚውና ዋነኛው እሴቱ ነው--መከላከያ ሚኒስቴር
Jun 10, 2023 56
አዲስ አበባ ሰኔ 03/2015(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ቁልፍ እሴት ከሆኑት ቀዳሚውና ዋናው ከራስ በፊት ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መቆም መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ዩኤስኤአይዲ (USAID) ሰሞኑን አጣርቻለሁ ብሎ ባወጣው መግለጫ ለሰብአዊ እርዳታ የመጣን እህል ከሌሎች መንግስታዊ አካላት ጋር በመሆን መከላከያ ሰራዊታችንም እንደተጠቀመ አድርጎ ያቀረበውን ሪፖርት የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ሲዘግቡት አስተውለናል ብሏል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራና ዘመናዊ መሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ ሰብዓዊ ድጋፍ የሚደረግላቸውን ወገኖቹን ቀለብ ሊቀማ ቀርቶ፤ ከቀለቡ ቀንሶ የሚያካፍል ሰራዊት መሆኑን የሃገሩ ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ በአጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሰላም ማስከበር በተሰማራባቸው ቦታዎች ሁሉ የተመሰከረለት መሆኑን ገልጿል። ኢትዮጵያ ለሰራዊቷ ደመወዝና ቀለብ መስጠት በመጀመር ቀዳሚ ነን ከሚሉ ሃገራት ተርታ የምትሰለፍ ነፃ እና ታሪካዊት ሃገር መሆኗን በመግለጫው የጠቀሰው የመከላከያ ሚኒስቴር የሰራዊቱ ቀለብ ለሃገር ውስጥ ነጋዴዎች እድሉን በመስጠት በግልፅ ጨረታ ተወዳድረው ስንዴም ሆነ ሌሎች ምግብ ነክ ፍጆታዎች የሚቀርብለት በተሟላ አሰራር የሚመራ ሰራዊት ነው ብሏል። ዩኤስኤአይዲ በሠጠው መግለጫ መሠረት ምናልባት የመከላከያ አባል የሆነ ወታደር በማይመለከተው ገብቶ ከመዋቅር ውጪ ሕግ የማስከበር ሥራውን ተጠቅሞ ከሌቦች ጋር በመተባበር እርዳታ ተሰርቆ እንዲወጣ በግል የተባበረ ካለ እና ተጣርቶ ከተገኘ የአገር መከላከያ ሠራዊት አመራር የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቋል። መከላከያ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦ ከኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር የተሰጠ መግለጫ ሰኔ 03/2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ቁልፍ እሴት ከሆኑት ቀዳሚውና ዋናው ከራስ በፊት ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መቆም ነው፡፡ ዩኤስኤአይዲ (USAID) ሰሞኑን አጣርቻለሁ ብሎ ባወጣው መግለጫ ለሰብአዊ እርዳታ የመጣን እህል ከሌሎች መንግስታዊ አካላት ጋር በመሆን መከላከያ ሰራዊታችንም እንደተጠቀመ አድርጎ ያቀረበውን ሪፖርት የተለያዩ ሚዲያዎች ሲዘግቡት አስተውለናል፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራ ዘመናዊ ሰራዊት ነው፡፡ ሰብዓዊ ድጋፍ የሚደረግላቸውን ወገኖቹን ቀለብ ሊቀማ ቀርቶ፤ ከቀለቡ ቀንሶ የሚያካፍል ሰራዊት መሆኑን የሃገሩ ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ በአጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሰላም ማስከበር በተሰማራባቸው ቦታዎች ሁሉ የዕለት ከዕለት ተግባሩ መሆኑን የደረሰላቸው ህዝቦች፤ መንግስታት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሁሉ የሚያውቁት ሰመ ጥር ህዝባዊ ሰራዊት ነው፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ ለሰራዊቷ ደመወዝና ቀለብ መስጠት ከጀመረች፤ ቀዳሚ ነን ከሚሉ ሃገራት ተርታ የምትሰለፍ ነፃ እና ታሪካዊት ሃገር ናት፡፡ ሰራዊታችን ዘመናዊ ነው ከሚያስብሉት አንዱ ደግሞ ይኸው ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው የሎጂስቲክ ግዥ እና አቅርቦት ጉዳይ ነው፡፡ የሰራዊታችን ቀለብ ለሃገር ውስጥ ነጋዴዎች እድሉን በመስጠት በግልፅ ጨረታ ተወዳድረው ስንዴም ሆነ ሌሎች ምግብ ነክ ፍጆታዎች የሚቀርብለት በተሟላ አሰራር እና አመራር የሚመራ ሰራዊት ነው፡፡ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት፡- 1ኛ/ ሠራዊታችን በቂ ሎጄስቲክ ያለው በዓለም አቀፍና በአገር ውስጥ ለተፈናቀሉትና በድርቅ ለተጎዱት በዓይነትና በገንዘብ የሚረዳ እንጂ ተቸግሮ ከአሰራር ውጭ የሚጠቀም አይደለም። 2ኛ/ ሠራዊታችን ማንኛውንም ዓይነት ምግብ በበጀቱ በሕግና በግልፅ ጨረታ ገዝቶ የሚጠቀም እንጂ ተቸግሮ የሕዝብ እርዳታ አካባቢ ሄዶ እርዳታ ላይ የሚሻኮትበት ዓይነት ድህነት የለበትም። ጥቆማ የሰጠ አካል እንኳ ቢኖር እስኪጣራ ሳይጠበቅ፤ እንደ ተቋምና እንደ ሠራዊት ስም የሚያጠፋ የሚዲያ ሽፋን መስጠት የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት ክብር ይነካል። 3ኛ/ ምንም እንኳን አገራችን በሚሊዮን የሚቆጠር እርዳታ ጠባቂ ሕዝብ ቢኖራትም ሠራዊቷን መመገብ የምትችልና በቂ ምግብና በጄት በመመደብ ሠራዊቱ ራሱ በሕግና በተቋም ሎጂስትክ አማካኝነት የምትመግብ አገር ናት። ሠራዊታችንም ኩሩና የችግረኞችን ስንዴ የማይሻማ ፕሮፌሽናል ሠራዊት ነው። ስለሆነም የእርዳታ ስንዴ የሚጠቀም ተቋም ወይም ዩኒት ወይም ወታደር የለንም። 4ኛ/ ዩኤስኤአይዲ (USAID) በሠጠው መግለጫ መሠረት ምናልባት የመከላከያ አባል የሆነ ወታደር በማይመለከተው ገብቶ ከመዋቅር ውጪ ሕግ የማስከበር ሥራውን ተጠቅሞ ከሌቦች ጋር በመተባበር እርዳታ ተሰርቆ እንዲወጣ በግል የተባበረ ካለ እና ተጣርቶ ከተገኘ የአገር መከላከያ ሠራዊት አመራር የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል። መከላከያ ሰራዊት ለሃገሩም ሆነ ለዓለም አቀፍ ሰላም መከበር መሰዋትነት የሚከፍል ምስጉን ሰራዊት ሆኖ እያለ፤ በአገራችን ውስጥና በውጪ አገር ያሉ ጥቂት የአገር መከላከያ ሠራዊት ጥላቻ ያላችው ፅንፈኞች እንዳሉ እናውቃለን። መካላከያን የማጠልሸት ሥራ የቆየና የለመድነው ነው። የመከላከያ ሠራዊታችንን ህዝባዊ ተፈጥሮ፣ አሰራርና ሥርዓት ሳይታወቅና መረጃ እንኳ ቢመጣ፤ አጣርቶ ሳይታወቅ፤ መረጃ የቀረበበት አካል ሳይጠየቅ፤ የሚዲያ ሽፋን መሰጠት ትክክል አይደለም ብለን እናምናለን። የሚመለከታቸው የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶችና የኢትዮጵያ መንግሥት እንዲያጣሩ እንተባበራለን። ከተጣራ በኋላ ሁሉንም ለሕዝብ ይፋ እናደርጋለን። የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር
የሀገር አቀፍ ሕግ አውጪዎች የጋራ የምክክር መድረክ በጅግጅጋ ይካሄዳል
Jun 9, 2023 95
ጅግጅጋ ሰኔ 2/2015(ኢዜአ)፦ የሀገር አቀፍ ሕግ አውጪዎች የጋራ የምክክር መድረክ ነገ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እንደሚካሄድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉበዔ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ፣በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ፣ የፍትሕ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ፣ የፌዴራል፣ የክልል እና የሁለቱ ከተማ መስተዳደር ምክር ቤቶች አፈ-ጉባዔዎች ማምሻውን ጅግጅጋ ከተማ ገብተዋል። የሕግ አውጪዎቹ ጅግጅጋ ሲደርሱ በሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ዑመር እና በክልሉ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ የሚካሄደው መድረክ በፌዴራል እና በክልል መንግሥታት፣ እንዲሁም በክልሎች መንግስታት መካከል ያለው ግንኙነት ጥንካሬዎች ለማስቀጠል እና የሚያጋጥሙ ክፍተቶችን ለመሙላት ያለመ ነው። በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን፣ ዋስትና ያለው የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለማረጋገጥ፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ልማትን ለማስቀጠል የመድረኩ ፋይዳ የጎላ እንደሚሆን በሕዝብ ተወካዮች ምከር ቤት የሚዲያ ዘርፍ ዳይሬክተር ወይዘሮ ብስራት ሽፈራው ገልጸዋል።
የሩሲያና የኢትዮጵያ አጋርነትን በተለያዩ የትብብር መስኮች ለማጠናከር እየተሰራ ነው - አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን
Jun 9, 2023 69
አዲስ አበባ ሰኔ 2/2015(ኢዜአ):- ለረጅም ዓመታት የዘለቀውን የኢትዮጵያና የሩሲያ ወዳጅነት በተለያዩ የትብብር መስኮች ይበልጥ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን ተናገሩ። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን ለኢዜአ እንደገለጹት ሁለቱ አገራት ለበርካታ ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት አላቸው። የኢትዮ-ሩሲያ የመንግሥትና የሕዝብ ለሕዝብ ወዳጅነት የጋራ ጥቅምን እንዲሁም መተማመንን መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። እያደገ የመጣውን የሁለቱ አገራት አጋርነት በኢኮኖሚ የትብብር መስክ ይበልጥ ሊያዳብሩ የሚችሉባቸው ዕድሎች መኖሩንም ነው የገለጹት። ይህንንም ተከትሎ አገራቱን በምጣኔ ኃብት መስክ ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ሰላም ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና መረጋጋት ትልቅ ትሩፉት እንዳለው ጠቁመው የኢትዮጵያ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም በሰላም ግንባታና በሌሎች ተያያዥ ሥራዎች ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸዋል። አገራቱ የሁለትዮሽ ብቻ ሳይሆን በባለብዙ ወገን መድረኮችም ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቁመው ይህንን ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል ነው ያሉት። በሌላ በኩል ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ጋር ያላትን አጋርነት ለማጠናከር እንደምትሰራ ገልጸዋል። በተለይም በአፍሪካ ኅብረት ትኩረት የተሰጠው 'ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ' መርህ እውን እንዲሆን አገራቸው ጽኑ እምነት አላት ብለዋል። ኢትዮጵያና ሩሲያ ከ125 ዓመታት በላይ ወዳጅነት ያላቸው አገራት ናቸው።
ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማሻገር የአሁኑ ትውልድ በዘመኑ ጠንክሮ መስራት እንዳለበት ተመለከተ
Jun 9, 2023 72
ሰኔ 02/2015 (ኢዜአ) ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች አገር ለማሻገር የአሁኑ ትውልድ በዘመኑ ያሉትን ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎችን በበጎ ተጠቅሞ ጠንክሮ መስራት እንዳለበት ተመለከተ። 32ኛው የጉሚ በለል የውይይት መድረክ "ቃል እና ተግባር፡ ከትውልድ እስከ ትውልድ” በሚል መሪ ሃሳብ በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ተካሄዷል፡፡ በውይይቱ ላይ የተገኙት የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሃይሉ አዱኛ ፤ የአንድን ትውልድ ማንነትና ምንነት የሚወስኑት ትውልዱ በዘመኑ ያሉ ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎችን ለመሻገር የሚያደርጋቸው ጥረቶች ናቸው" ብለዋል። "ሀገር በትውልድ ቅብብሎሽ ይገነባል" ያሉት አቶ ሃይሉ፤ ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ሀገር ማሻገር የሚቻለው የአሁኑ ትውልድ በዘመኑ ያሉትን አማራጮች ተጠቅሞ ጠንክሮ ሲሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የመድረኩ መሪ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ብርሃኑ ሌንጂሶ በበኩላቸው በትልቁ የሚገነባው ማህበራዊ እሴት መነሻው ሰው ለራሱ ከሚገባው ቃል ኪዳን ነው ብለዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ትውልድም በቃሉ ላይ የተመሰረተ የሀገር ግንባታ እንደሚያካሄድ ተናግረዋል። በመድረኩ የመነሻ የውይይት ጽሁፍ ያቀረቡት በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ዮሴፍ ቤኮ የተገባው ቃል በድርጊት የማይገለጽ ከሆነ እንደባከነ ይቆጠራል ብለዋል። ቃል እና ተግባር እንደ ሰንሰለት የተሳሰረ ያሉ ሲሆን ትውልድም ካለፈው ከአሁኑና ከሚመጣው ጋር የተሳሰረ ነው ብለዋል። በዚህም የመደመር ትውልድም ካለፈው የተገኘውን በጎ ውጤት እንደ ስንቅ በመያዝ ለሚመጣው ትውልድ ቃሉን ወደ ተሻለ ድርጊት መቀየር እንዳለበት በመግለጽ። በውይይቱ ላይ ተሳታፊ ከነበሩት ተማሪዎች መካከል ከአምቦ ኢፈ ቦሩ 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምርት ቤት የመጣችው የ9ኛ ክፍልተማሪ ፅዮን ሁምኔሳ በሰጠችው አስተያየት፤ "እኛ የመደመር ትውልድ የቃል ብቻ ሳንሆን የተግባር ትውልድ መሆናችንንም ጠንክረን በመስራት እናስመሰክራለን ብላለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በመደመር ትውልድ መጽሓፋቸው አንድ ትውልድ በዘመኑ ያሉ ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎችን ለመሻገር የሚያደርጋቸው ጥረቶች ከግምት በማስገባት ስለ ትውልዱ ያሰፈሩት ሀሳብ በመድረኩ ተወስቷል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር መጻሕፍት ኢትዮጵያን ለማስቀጠል መሰረት የሚጥሉ እሳቤዎችን የያዙ ናቸው - አርቲስት ደበበ እሸቱ
Jun 9, 2023 265
አዲስ አበባ ሰኔ 2/2015(ኢዜአ)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሶስቱ የመደመር መጻሕፍት ኢትዮጵያን ለማስቀጠል መሰረት የሚጥሉ እሳቤዎችን የያዙ መሆናቸውን አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ገለጹ። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አዘጋጅነት "የመደመር ጉዞ" በሚል መሪ ሀሳብ በቢሾፍቱ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። በውይይቱም የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች አካላት ተሳትፈዋል። የመደመር እሳቤ ይዟቸው የመጡ መልካም አጋጣሚዎች፣ በሂደቱ እያጋጠሙ የሚገኙ ተግዳሮቶችና መፍትሔ አመላካች ጉዳዮችን የሚዳስሱ የማጠንጠኛ ሀሳቦች ላይ ምክክር ተደርጓል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የመደመርን ፋይዳ የሚያመላክቱ እሳቤዎችን ያካተቱ ሶስት መጻህፍት ለንባብ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። የስራ ባህልን ለማጎልበት እና በስራ ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን መፍትሔ ለመስጠት አመላካች ሀሳቦችን መካፈል የውይይቱ ዓላማ መሆኑን አመልክተዋል። የመደመር እሳቤ የሚቆም ሳይሆን ቀጣይነት ያለው ሂደት እንደሆነም ተናግረዋል። የመድረኩ ተሳታፊ አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ያለፈውን ዘመንና የአሁኑን ትውልድ ጉዞ እና ተሞክሮ አቅርበዋል። ጭፍን ጥላቻ እና ትችትን በማስወገድ የተሰነዱ መጻሕፍት አንብቦ በሚገባ አሰናስሎ መገንዘብ እና መረዳት ያስፈልጋል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሶስቱ የመደመር እሳቤ መጻሕፍት ቀጣይ የኢትዮጵያን እጣ ፋንታ ለመወሰን መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በውይይቱም የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የስራ ባህልን በማሻሻል ውጤታማ የልማት ምህዳርን መፍጠር እንደሚገባ ተገልጿል። እያንዳንዱ ዜጋ በስራ ሂደት የተሻለ ትጋት እና ተነሳሽነትን በመላበስ ኢትዮጵያ ያላትን ጸጋ አልምቶ በመጠቀም እድገትና ብልጽግናዋን ማስቀጠል እንደሚያስፈልግም ተጠቁሟል።
ማህበራዊ
የተማርንበትን ትምህርት ቤት ለማዘመንና የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚደረገውን ጥረት ይበልጥ እናግዛለን- የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች
Jun 10, 2023 35
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፡- የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤትን ለማዘመንና የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ ለሚደረገው ጥረት ያላሰለሰ ድጋፍ እንደሚያደርጉ የቀድሞ ተማሪዎች ገለጹ። በ1917 ዓ.ም. እንደተመሰረተ የሚነገርለት ፋና ወጊው የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የአሁኑ ደግሞ የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንድ ክፍለ ዘመኑን ሊደፍን ሁለት ዓመታት ብቻ ቀርተውታል። ትምህርት ቤቱ ለአገሪቱ የሥልጣኔ ጉዞ ትልቅ ሚና ማበርከቱን በርካቶች ይናገሩለታል። የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪ አርቲስት ደበበ እሸቱ ትምህርት ቤቱ ለአገርና ለወገን የጠቀሙ በርካታ ምሁራንን አፍርቷል ብሏል። በየዘመኑ ከትምህርት ቤቱ የወጡ ሰዎች በተለያዩ ሙያ ዘርፎች ፈርጦች ሆነው አገራቸውን ማገልገላቸውን ገልፆ፤ ትምህርት ቤቱ እውቀትንና ክህሎትን ከማስጨበጥ ባለፈ ተማሪዎች በመልካም ሥነ-ምግባር ታንጸው እንዲወጡ በማድረግ ረገድ አስተዋጽዖ እንዳላቸው ተናግሯል። የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪዎች ማኅበር በማቋቋም ትምህርት ቤቱን በተለያዩ ዘርፎች እየደገፉ እንደሚገኙ ገልፆ፤ ይህም ለትምህርት ጥራት መምጣት የራሱ የሆነ አበርክቶ ይኖረዋል ነው ያለው። ሌላኛው የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪ ካፒቴን ከበደ ወልደፃዲቅ፤ ማኅበሩ ትምህርት ቤቱ የሚያስፈልጉትን አንዳንድ የትምህርት ቁሳቁስ መሣሪያዎችን ድጋፍ በማድረግ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል። በተለይም ለመማር ማስተማር አገልግሎቱ ጠቀሜታ ያላቸውን የኮምፒውተር ክፍሎች ከማደራጀት ባለፈ በማዕድ ማጋራትና ለተማሪዎች አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በማሟላት ለኮሌጁ እገዛ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ ጋረደው አጥናፍ እና ሰዓሊ ሉዑልሰገድ ረታ የተባሉ የቀደሞ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በበኩላቸው፤ ትምህርት ቤቱ በግብረገብነትና ሥነ-ምግባር አስተምህሮ ላሉበት ደረጃ ያበቃቸው በመሆኑ አሁን ያለው ተተኪ ትውልድ በተመሳሳይ ለስኬት እንዲበቃ ትምህርት ቤቱን መርዳትና መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። በመሆኑም እነርሱ በትምህርት ቤቱ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ትምህርት ለአንድ አገር እድገት ወሳኝ በመሆኑ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የተጀመረውን ሥራ ውጤታማ ለማድረግ የቀድሞ ተማሪዎች ያስተማራቸውን ትምህርት ቤት መርዳትና መደገፍ አለባቸው ሲል አርቲስት ደበበ እሸቱ ተናግሯል። ካፒቴን ከበደ በበኩላቸው፤ የቀድሞ ተማሪዎች ያስተማራቸውን ትምህርት ቤት ተመልሰው በመደገፍ የትምህርት ጥራት እንዲመጣ አስተዋጽዖ ማድረግ እንደሚገባቸው ነው የተናገሩት። አቶ ጋረደው አጥናፍ እና ሰዓሊ ሉዑልሰገድ ረታ በበኩላቸው፤ የአገር እድገት መሠረት የሆኑትን ትምህርት ቤቶች መደገፍ የውዴታ ግዴታ መሆኑን ጠቁመዋል። በመሆኑም የቀድሞ ተማሪዎች ያስተማራቸውን ትምህርት ቤት በመደገፍ የትምህርት ጥራት እንዲጠበቅ ያላሰለስ ድጋፍ ማድረግ አለባቸው ብለዋል። የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ተሾመ ፈይሳ በበኩላቸው፤ የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪዎች ለመማር ማስተማሩ ከሚያደርጉት እገዛ ባሻገር ለተማሪዎች ሞራል ግንባታ አዎንታዊ አስተዋጽዖ እያበረከቱ እንደሚገኙ አንስተዋል። በመሆኑም ይህን ጥሩ ተሞክሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች በማስፋት የቀድሞ ተማሪዎች የተማሩበትን ትምህርት ቤት እንዲደግፉ በማድረግ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት በሚደረገው ጥረት የራሳቸውን ጉልህ ሚና እንዲወጡ ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት።
የተጀመረው የፍትህ ተቋማት የለውጥ ፍኖታ ካርታ ትግበራ በትኩረት ሊሰራ ይገባል--አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jun 10, 2023 36
ጅግጅጋ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦ ፍትህ ለሰላም፣ ለዘላቂ ልማትና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዋሳኝ ሚና ስላለው የተጀመረው የፍትህ ተቋማት የለውጥ ፍኖታ ካርታ ትግበራ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። 3ኛው ሀገር አቀፍ የህግ አውጪዎች የጋራ የምክክር መድረክ በጅግጅጋ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንደተናገሩት መድረኩ በመንግስታት መካከል ያለውን ግንኙነት ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1231/2013 መሰረት በማድረግ በፌዴራል እና በክልሎች መካከል ያለ ግንኙነትን ለማጠናከር በየስድስት ወሩ የሚካሄድ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ፍትህ ለማረጋገጥና ለማጠናከር በፌዴራል የፍትህ ተቋማት የተጀመረው የፍትህ የለውጥ ፍኖታ ካርታ በየደረጃው ያሉ የፍትህ ተቋማት ለመተግበር መስራት ይገባቸዋል ብለዋል። "ፍትህ ለሰላም፣ ለዘላቂ ልማት፣ ለፖለቲካና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና አለው" ሲሉም አፈ-ጉባኤው ተናግረዋል። በህግ አውጪዎች መካከል የሚደረገው ውይይት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን፣ ዋስትና ያለው ዲሞክራሲ ለማረጋገጥ እና ፈጣን እድገት በማስመዝገብ፣ አንድ የፖለቲካ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመፍጠር ያግዛልም ብለዋል። የክልሎች እና የብሄረሰቦች ምክር ቤቶች እየተሳተፉበት በሚገኘው የምክክር መድረክም የእርስ በእርስ ግንኙነትን ከማጠናከር ባሻገር መልካም ተሞክሮዎች የሚለዋወጡበት እንደሆነም ጠቁመዋል። መድረኩ በፌዴራል ደረጃ በፍትህ ስርዓቱ ላይ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በክልሎችም ለማጠናከር የሚያግዝ ምክክር ይካሄድበታል ተብሏል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ፣ "እውነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት በየደረጃው የሚገኙ የፍትህ ተቋማት ተቋማዊ ነፃነታቸው ተጠብቆ በሰው ኃይል እና በቴክኖሎጂ ታግዘው መስራት ይጠበቅባቸዋል" ብለዋል። በሶማሌ ክልልም ከለውጡ በፊት የነበረ ሰፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስቀረት ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል፣ በዚህም ውጤቶች ታይተዋል ሲሉ ገልጸዋል። ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው መድረክ የፍትህ ተቋማት የለውጥ ፍኖታ ካርታ ስርዓት የጋራ ሰነድ እንዲሁም የፍርድ ቤቶች የአሰራር ለውጥ ላይ ያተኮረ ፍኖተ ካርታ ቀርቦ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል። በመድረኩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌደሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ቴዎድሮስ ምህረት፣ የፍትህ ሚኒስትር ዶክተር ጌድዮን ጢሞቲዎስ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ እና የክልል፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር እና የተለያዩ ብሄረሰቦች ምክር ቤቶች አፈ-ጉባኤዎች እና ምክትል አፈ-ጉባኤዎች ተገኝተዋል።
11ኛው የቱሪዝም ጥናትና ምርምር ጉባኤ በጂንካ ከተማ እየተካሄደ ነው
Jun 10, 2023 45
ጂንካ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦ በቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩትና በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የተዘጋጀው 11ኛው ዓመታዊ የቱሪዝም ጥናትና ምርምር ጉባኤ በጂንካ ከተማ እየተካሄደ ነው። የዘንድሮው የቱሪዝም ዓመታዊ የጥናትና ምርምር ጉባኤ "ብዝሃነትና ዘላቂ የቱሪዝም ልማት ለስራ እድል ፈጠራ'' በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ በቱሪዝም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። በቱሪዝም መስክ ያለውን እምቅ ሀብት ጥቅም ላይ ለማዋል ጥራቱን የጠበቀ የክህሎት ስልጠና መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል። ''የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ የሰለጠነና የበቃ የሰው ሃይል ይፈልጋል'' ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የሰው ሀይሉን በስልጠና በማብቃትና በቴክኖሎጂ በማገዝ ዘርፉን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኩሴ ጉድሼ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የብዝሃ-ባህልና የቱሪዝም መስኩን እንደ አንድ የልህቀት ማዕከል አድርጎ በመሥራት ላይ ይገኛል ብለዋል። በጉባኤው ላይ የሚቀርቡ የጥናትና ምርምር ውጤቶችም ዩኒቨርሲቲው በቱሪዝም መስክ ለሚያከናውናቸው ሥራዎች አጋዥ እንደሚሆኑ ተናግረዋል። በጉባኤው “በቱሪዝም መስክ ያሉ እድሎችና ፈተናዎች”እንዲሁም “የክህሎት ስልጠና ለዘላቂ የቱሪዝም እድገት” በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር ይደረጋል። የፌዴራልና የክልል የዘርፉ አስፈጻሚዎችና ባለድርሻ አካላት፣ የሆቴልና ቱሪዝም ድርጅቶች፣ የትምህርት ስልጠና ተቋማትና የሙያ ማህበራት ተወካዮች በጉባኤው ላይ ተገኝተዋል።
የሴቶች ውክልና በቁጥር ብቻ መተርጎም የለበትም--ፕሬዚደንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ
Jun 10, 2023 52
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦የሴቶች ውክልና በቁጥር ብቻ መተርጎም የለበትም ሲሉ ፕሬዚደንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ ተናገሩ። 10ኛው የሴት የፖለቲካ መሪዎች ድርጅት ዓመታዊ ጉባዔ በአውሮፓ ህብረት ፓርላማ እና በቤልጂየም ፌዴራል ፓርላማ “ውክልና ወሳኝ ነው” በሚል መሪ ሀሳብ በጋራ ተካሂዷል። የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ “ውክልና ወሳኝ ነው“ በሚል መሪ ሃሳብ በተጀመረው ጉባኤ ዋዜማ ላይ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። በንግግራቸውም ሴቶች በሰላም እና ደህንነት ዙሪያ ስለሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች እና የሴቶች ውክልና በቁጥር ብቻ መተርጎም እንደሌለበት ተናግረዋል። በጉባኤው ላይ ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ የ“ፈር ቀዳጅ ሴት” እውቅና ተበርክቶላቸዋል። ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ በቤልጂየም ፓርላማ በተካሄደውና ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች አመራር ሴቶች በተገኙበት የሴት ፖለቲካ መሪዎች ድርጅት ዓመታዊ ጉባዔ ላይ ነው እውቅናው የተበረከተላቸው። እውቅናው በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሴት ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸውን ጨምሮ ቀደም ሲል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በተለያዩ የስራ ዘርፎች በነበራቸው ከፍተኛ የኃላፊነትና የመሪነት ሚና ፈር ቀዳጅ በመሆናቸውም ጭምር ያገኙት መሆኑ ተገልጿል። ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር “ሽልማቱ ለብርቱዎቹ ሴቶች፣ በመጠለያ ጣቢያዎች ላሉት፣ ሕክምና ላይ ሆነው ሲጎበኟቸው የመማር ጉጉት እንዳላቸው ለነገሯቸው፣ ብቻቸውን ቤተሰብ የማስተዳደር ኃላፊነት ለተጣለባቸው እና ተስፋ ለሚሰጡን ባለ ተሰጥኦ የሀገሬ ሴቶች ይሁንልኝ” ብለዋል። የዘንድሮው ጉባኤ አስተናጋጅ ሀገር ቤልጂየም በአሁኑ ጊዜ በሴቶች አፈ ጉባኤዎች የሚመሩ ሁለት ምክር ቤቶች እንዳሏት ከፕሬዚደንት ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ኢኮኖሚ
ጫናን መቋቋም የሚችል ኢኮኖሚ ለመገንባት የታክስና ጉምሩክ ሕግ ተገዢነትን ማስፈን ይገባል - ገቢዎች ሚኒስቴር
Jun 10, 2023 26
ሀዋሳ ሰኔ 3/2015 (ኢዜአ)፡- ጠንካራና ጫናን መቋቋም የሚችል ሀገራዊ ኢኮኖሚ ለመገንባት የታክስና ጉምሩክ ሕግ ተገዢነትን ማረጋገጥ ከሁሉም ባለድርሻዎች የሚጠበቅ ኃላፊነት እንደሆነ የገቢዎች ሚኒስቴር ገለጸ። የደቡብ ክልል ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የዕውቅናና ሽልማት መርሀ ግብር የክልልና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በቡታጅራ ከተማ ተካሂዷል። በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የገቢዎች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ቱሉ የግብር ሥርዐቱን በማክበርና በማስከበር ጠንካራና ጫናን መቋቋም የሚችል ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ኢኮኖሚ መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል። በመሆኑም ጠንካራ የታክስ ሥርዐትን መገንባትና የታክስና ጉምሩክ ሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻዎች በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በሀገር ደረጃ ይህንን ለማሳካት የሚያስችል ከየካቲት 2015 ዓ.ም እስከ የካቲት 2016 ዓ.ም የሚቆይ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ተገዢነት ንቅናቄ "ግብር ለሀገር ክብር" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታውሰዋል። የደቡብ ክልል ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮችን ዕውቅናና ሽልማት የመስጠት መርሀግብርም የዚሁ ንቅናቄ አካል እንደሆነ ጠቅሰዋል። የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው ከውጭ እርዳታና የኢኮኖሚ ጫና ተላቀን ሀገራችንን በራሳችን አቅም ማሳደግና ማልማት የምንችለው የውስጥ ገቢያችን ላይ በትኩረት መሥራት ስንችል ነው ብለዋል። ለዚህም የተፈጥሮና የሰው ሀይል ፀጋዎችን ተጠቅሞ ኢኮኖሚን ማሳደግና ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት ተገቢውን ግብር በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ የተመዘገበውን የኢኮኖሚ ዕድገት በመጠቀም ገቢውን ማሳደግ እንደተቻለ ጠቅሰው፤ የክልሉ ገቢ ላለፉት አራት ዓመታት በአማካይ ከ30 በመቶ በላይ እያደገ መምጣቱን አስረድተዋል። በትኩረትና በታማኝነት መስራት ከተቻለ ከዚህ በላይ ወጪውን መሸፈንና የልማት ሥራዎችን በአግባቡ ለመስራት የሚያስችል ገቢ መሰብሰብ እንደሚቻል ጠቁመዋል። ግብር ከፋዩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን በማሳደግ የተሻለ ገቢ ማስገኘት እንዲችል ከመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች ጀምሮ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች በፍጥነት ወደ ሥራ ገብተው ገቢ ማመንጨት እንዲችሉ ማድረግና ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ከመንግስት አካላት የሚጠበቅ ተግባር እንደሆነ ገልፀዋል። ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር በታማኝነት መክፈላቸውን አጠናክረው በማስቀጠል በሀገራቸው ልማትና እድገት የበኩላቸውን አሻራ እንዲያኖሩ ጥሪ አቅርበዋል። ከተሸላሚ ግብር ከፋይች መካከል በዲላ ከተማ በዱቄት ፋብሪካ፣ በቡና ንግድና ሌሎች ሥራዎች የተሰማሩት አቶ የሱፍ ጠሀ 7 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ግብር በመክፈል ተሸላሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለ14 ዓመታት ያህል ግብር በታማኝነት በመክፈል ሲሸለሙ መቆየታቸውን ጠቅሰው፤ መሸለሜ በመንግስትና ህዝብ ዘንድ ከማገኘው ክብርና ፍቅር ባሻገር ለሀገሬ እድገት የሚጠበቅብኝን በማድረጌ ደስተኛ ያደርገኛል ብለዋል። ለሀገር የሚገባውን ግብር በታማኝነት መክፈል ጥቅሙ ለራስ እንደሆነም ተናግረዋል። በመርሀግብሩ ላይ 58 ለታክስ ህግ ተገዢና ታማኝ የሆኑ ግንባር ቀደም ግለሰብ ግብር ከፋዮች፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶች እና ሴክተር መስሪያ ቤቶች ዕውቅናና ሽልማት የተሰጣቸው ሲሆን ከ50 ሺህ 310 ብር እስከ 17 ሚሊዮን 914 ሺህ 763 ብር ድረስ ግብር የከፈሉ በደረጃ ሐ፣ ለ እና ሀ ግለሰብ ግብር ከፋዮች ተሸላሚ ሆነዋል።
በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ካለፈው ዓመት የዞረውን ጨምሮ 6 ሺህ 269 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ቀርቧል
Jun 10, 2023 37
ሰቆጣ ሰኔ 03/2015 (ኢዜአ) በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር 6 ሺህ 269 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መቅረቡን የአስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የቀረበው የአፈር ማዳበሪያ ከፍላጎቱ አንጻር ሰፊ ክፍተት ያለበት በመሆኑ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በአማራጭነት አርሶ አደሩ እንዲጠቀም ተጠይቋል። የመምሪያው ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በብሄረሰብ አስተዳደሩ ለመጪው የምርት ዘመን 19 ሺህ 560 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል። በክልሉ በሚስተዋለው ማዳበሪያ እጥረት ለመፍታት 11 ሺህ 148 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እንደሚቀርብ የተገለጸ ቢሆንም እስካሁን የቀረበው 3 ሺህ 359 ኩንታል ብቻ መሆኑ አሳሳቢ ነው ብለዋል። ችግሩን ለመፍታት በተደረገው ጥረት ካለፈው ዓመት የዞረውን ጨምሮ 6 ሺህ 269 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ተናግረዋል። አርሶ አደሮች እስከ ሶስት ጊዜ መሬቱን ደጋግመው በማረስ ያዘጋጁ ቢሆንም የአፈር ማዳበሪያ እጥረት የእርሻ ስራውን እንዳያስተጓጉልባቸው መስጋታቸውን አመልክተዋል። ለክልሉ በቅርቡ ከሚገባው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ ለብሄረሰብ አስተዳደሩ ሲደርስ ለአርሶ አደሩ በፍጥነት በማሰራጨት ዘሩን እንዲዘራ እንደሚደረግ አስረድተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ያጋጠመውን የማዳበሪያ እጥረት አርሶ አደሩ ተገንዝቦ ባለፈው በጋ ያዘጋጀውን 733 ሺህ ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በአግባቡ ተጠቅሞ እንዲዘራ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። የተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያም 120 ሺህ ሄክታር መሬት መሸፈን የሚችል መሆኑን ጠቁመው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ፈጥነው የሚበሰብሱ እጸዋቶችንና ፍግን በመጠቀም ተጨማሪ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት እንዲጠቀሙ መክረዋል። የብሄረሰብ አስተዳደሩ ምክትል አስተዳዳሪና የኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሹመት ጥላሁን የተከሰተውን የማዳበሪያ እጥረት ለመቅረፍ አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ መጠቀም እንዳለበት አስገንዝበዋል። በጋዝጊብላ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ወዳጅ ጌታሁን እንዳሉት፤ የማዳበሪያ አቅርቦት ችግር በመኖሩ በግብርና ስራቸው ላይ መስተጓጎል ገጥሟቸዋል። የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ በማቅረብ የመኸር እርሻቸውን በወቅቱ እንዲያከናውኑ የሚያስችል ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል። በሰቆጣ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር በሩ ፈንታ በበኩላቸው ማሳቸውን በአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት ምክንያት ማረስ እንዳልቻሉ ተናግረዋል። በብሄረሰብ አስተዳደሩ በ2015/16 የምርት ዘመን ከ120 ሺህ 638 ሄክታር መሬት በሰብል በመሸፈን ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን የመምሪያው መረጃ ያመለክታል።
በትግራይ ክልል ከተሞችን መልሶ ለመገንባት የፌደራል መንግስት ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር ለመስራት መንቀሳቀስ ጀምሯል- ሚኒስቴሩ
Jun 10, 2023 45
መቀሌ ሰኔ 3 / 2015(ኢዜአ) ፡- በትግራይ ክልል በነበረው ችግር ጉዳት የደረሰባቸውን ከተሞች መልሶ ለመገንባት ከአለም ባንክና ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር በቅንጅት ለመስራት እንቅስቃሴ መጀመሩን የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ ከተባባሪ አካላት ጋር በመሆን በከተሞች መልሶ ግንባታ፤በወጣቶችና ሴቶች ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ላይ ከክልሉ ለተወጣጡ የከተማ ልማት አመራሮችና ባለሙያዎች በመቀሌ ከተማ ያዘጋጀው ስልጠና ተጀምሯል። በስልጠናው መድረክ ላይ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተማ ልማትና ቤቶች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሄለን ደበበ እንዳሉት፤ በነበረው ችግር በትግራይ ክልል ጉዳት ከደረሰባቸው አንዱ የከተማ መሰረተ ልማት ነው። ጉዳት የደረሰባቸውን ከተሞች መልሶ በመገንባት በዘርፉ የወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የፌዴራል መንግስት ከዓለም ባንክና ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር ተቀናጅቶ ለመስራት መንቀሳቀስ ጀምሯል ብለዋል። በትግራይ ክልል ጉዳት የደረሰባቸውን ከተሞች መልሶ ለመገንባት በሚደረገው እንቅስቃሴ በየከተማው የተመደቡ አመራሮችና ባለሙያዎች የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ እንዳለባቸው አመልክተዋል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የከተማ መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ አልማዝ ገብረፃዲቅ በበኩላቸው፤ የተጎዱ ከተሞችን መልሶ በማቋቋም የህዝቡን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ከፌዴራል መንግስት ጋር ተቀናጅቶ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቀዋል። በመቀሌ በተዘጋጀው የሶስት ቀናት ስልጠና ላይ ከትግራይ ክልል ዘጠኝ ከተሞች የተውጣጡ ከ100 የሚበልጡ የከተማ ልማት ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ኢዜአ ከሥፍራው ዘግቧል።
ኮሪያ ሪፐብሊክ የጫማ ምርት ዘርፍ ማሳደግ አላማ ላደረገው ፕሮጀክት የ10 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ልታደርግ ነው
Jun 10, 2023 47
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ):-ኮሪያ ሪፐብሊክ በኢትዮጵያ የጫማ ምርት ዘርፍን ማሳደግ አላማ ላደረገው ፕሮጀክት የ10 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እንደምታደርግ አስታወቀች። ፕሮጀክቱ በቡሳን ሜትሮፖሊታን ከተማ ይፋ ሆኗል። ‘ቡሳን ኢኮኖሚክ ፕሮሞሽን ኤጀንሲ’ በተሰኘው የጫማ ኢንዱስትሪ ማስተዋወቂያ ማዕከል አማካኝነት የሚተገበረው ፕሮጀክት በጫማ ምርት ዘርፍ የኢትዮጵያን አቅም መገንባት ላይ ያተኮረ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ፕሮጀክቱ ከእ.አ.አ 2023 እስከ 2027 የሚተገበር ሲሆን ለጫማ አምራቾች ድጋፍና ስልጠና በመስጠት በኢትዮጵያ የቆዳ እና የቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ በተለይም የጫማ ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን የመጨመር ግብ እንዳለው ገልጿል። የኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ(ኮይካ) ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚያስፈልገውን የ10 ሚሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚሸፍንም ተመላክቷል። በኮሪያ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ሁለቱ አገራት ያላቸውን ለረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ወዳጅነት አንስተዋል። የአገራቱ ግንኙነት በፖለቲካ እና ኢኮኖሚው መስክ ይበልጥ የመጠናከር አቅም እንዳለው ገልጸው ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ያሉ የጫማ አምራቾች ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ካላት ወጣት የሰው ኃይል እና እምቅ ሀብት አኳያ በቆዳ እና ቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ የውጭ ኢንቨስትመንትን የተሻለ የመሳብ አቅም ባለቤት መሆኗን ተናግረዋል። አምባሳደር ደሴ ለ‘ቡሳን ኢኮኖሚክ ፕሮሞሽን ኤጀንሲ’ እና ቡሳን ሜትሮፖሊታን ከተማን ለፕሮጀክቱ እውን መሆን ላደረጉት ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ከአቅም ግንባታ ፕሮጀክቱ ይፋ ማድረጊያ መርሐ-ግብር ጎን ለጎን በኮሪያ ሪፐብሊክ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ‘ቡሳን ኢኮኖሚክ ፕሮሞሽን ኤጀንሲ’ በተሰኘው የጫማ ኢንዱስትሪ ማስተዋወቂያ ማዕከል የሁለቱን አገራት ትብብር ማጠናከር የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። በተጨማሪም አምባሳደር ደሴ ዳልኬ በቡሳን ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የጫማ ፋብሪካዎች እንዲሁም የጫማ ኢንዱስትሪ ማስተዋወቂያ ማዕከል ሰርቶ ማሳያ እና ስልጠና ማዕከል ጎብኝተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ምሁራን ለአገራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፍላጎት የሚያሟላ እውቀትና ክህሎት እንዲፈጠር የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ተጠየቀ
Jun 9, 2023 70
ዲላ ሰኔ 2/2015(ኢዜአ):- ምሁራን ለአገራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፍላጎት ምላሽ የሚሰጥ እውቀት እና ክህሎት እንዲፈጠር የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ። ዲላ ዩኒቨርሲቲ "ምርምር ለማህበረሰብ ለውጥ" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው 12ኛው አገር አቀፍ የምርምር አውደ ጥናት ዛሬ ተካሄዷል። የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አቢ ታደሰ ኢትዮጵያ ከፖሊሲ ማዕቀፍ ጀምሮ በሰው ሀብት ልማት እና የቴክኖሎጂ ልማት ላይ መዋለ ንዋይ በማፍሰስ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነች ነው ብለዋል። በግብርና መካናይዜሽን፣ በኢንዱስትሪ ልማት እንዲሁም ደመና የማበልጸግ ቴክኖሎጂን ጨምሮ በአየር ንብረት እና መሰል ዘርፎች ጥረት እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል። ይሁንና ሳይንስና ቴክሎኖጂን በሙሉ አቅም ተጠቅሞ ሁለንተናዊ ለውጥ በማረጋገጡ ረገድ ገና ብዙ መስራትን እንደሚጠይቅ አመልክተዋል። በመሆኑም በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ የመጠቀም ፍላጎት በሚያሟላ መልኩ ዓለም አቀፍ የእውቀትና የክህሎት ሽግግር እንዲፈጠር በትጋት መስራት ከምሁራን የሚጠበቅ ስራ መሆኑን ነው ፕሮፌሰር አቢ የገለጹት። ከማህበራዊ ለውጥ ጋር የተቆራኘ የምርምር ስራ ከማከናወን ባለፈ ልምድና ተሞክሮ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትስስር መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ጽዮን ሙላት በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ የሚገኙ ቴክኖሎጂዎች በዓለም አቀፍ ልምድ እና ተሞክሮ መዳበር እንዳለባቸው ገልጸዋል። የቴክኖሎጂ ውጤት የሆኑ የተለያዩ የሕክምና መሳሪያዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ በቅንጅት መስራት ይገባል ነው ያሉት። የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ሃብታሙ ተመስገን በግብርናው ልማት በተለይም በደጋ ፍራፍሬ እንዲሁም በቡና ልማት የተገኙ የምርምር ውጤቶች አርሶ አደሩን ተጠቃሚ እያደረጉ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም የምርምር ስራዎች ወደ ተግባር በመቀየርና ቴክኖሎጂ በማላመዱ ረገድ እየተከናወኑ የሚገኙ ጥረቶችን የሚያጠናከር ነው ብለዋል። በአውደ ጥናቱ ላይ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተወጣጡ ምሁራን የጥናት ውጤታቸውን ያቀረቡ ሲሆን የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘጠኝ የአውሮፓ ሕብረት ፕሮጀክቶችን አሸነፈ
Jun 9, 2023 71
አዲስ አበባ ሰኔ 2/2015 (ኢዜአ):- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአውሮፓ ሕብረት ከሚደግፋቸው 17 የምርምር እና የትምህርት ልህቀት ማዕከላት ፕሮጀክቶች መካከል በዘጠኙ አሸናፊ መሆኑን አስታወቀ። በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን እ.አ.አ ሕዳር 2022 የ ‘ARUA’ እና ‘Guild’ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች በነበራቸው ስብሰባ በአውሮፓ ሕብረት የሚደገፉ የምርምር እና የትምህርት ልህቀት ማዕከላት ለማቋቋም መወሰናቸው ይታወሳል። በዚሁ መሰረት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በርካታ ፕሮፖዛሎች የቀረቡ ሲሆን ባለፉት ሁለት ተከታታይ ቀናት በቤልጂየም ብራስልስ በተካሄደው ግምገማ መሰረት 17 የልህቀት ማዕከል ተመስርተዋል። ከነዚህ የልህቀት ማዕከል ፕሮጀክቶች ውስጥም በዘጠኙ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊ መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መረጃ አመልክቷል። በተጨማሪም የሁለት የፕሮጀክት ፕሮፖዛል ውጤት በመጪው ጥቂት ወራት እንደሚታወቅም ነው ዩኒቨርሲቲው ያስታወቀው። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና ይህ ውጤት ለዩኒቨርሲቲውም ሆነ ለአገር ትልቅ ፋይዳ ያለው ነው ብለዋል። ፕሮፌሰር ጣሰው ለተገኘው ውጤት አስተዋጽኦ ላደረጉ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች እንዲሁም በቤልጂየም ብራስልስ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የትምህርት ቤቶች የፈጠራ ውጤቶች ለሳይንስና ቴክኖሎጂ እድገት መሠረት የሚጥሉ በመሆኑ አስፈላጊው ድጋፍና እገዛ ይደረጋል- የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈጉባኤ
Jun 8, 2023 135
አዲስ አበባ ሰኔ 1/2015 (ኢዜአ) የትምህርት ቤቶች የፈጠራ ውጤቶች ለሳይንስና ቴክኖሎጂ እድገት መሠረት የሚጥሉ በመሆኑ አስፈላጊው ድጋፍና እገዛ የሚደረግ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ቡዜና አልከደር ገለጹ። 8ኛው ከተማ አቀፍ የተማሪዎችና የመምህራን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ አውደ-ርዕይ “በሳይንስ ቴክኖሎጂ ፈጠራ የዳበረ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ በወዳጅነት ፓርክ ተከፍቷል፡፡ በአውደ-ርዕዩ ላይ የመንግሥትና የግል ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችና መምህራን የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎቻቸውን ይዘው ቀርበዋል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ቡዜና አልከድር፤ አውደ-ርዕዩ የፈጠራ ውጤቶች የሚተዋወቁበት፣ ተወዳዳሪነት የሚጎለብትበትና የልምድ ልውውጥ የሚደረግበት መሆኑን ገልጸዋል። በተማሪዎችና መምህራን የሚቀርቡ የፈጠራ ሥራዎች ለሳይንስና ቴክኖሎጂ እድገት መሠረት የሚጥሉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም የአውደ-ርዕዩ መዘጋጀት ፈጠራን ለማስፋፋትና ፈጣሪዎችን ለማበረታታት የላቀ ትርጉም አለው ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ የፈጠራ ሥራዎቹ ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዲያድጉ የሚጠበቅበትን እገዛና ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የሳይንስና ፈጠራ ሥራን መሠረት በማስያዝ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥም የትምህርት ቤቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በበኩላቸው፤ በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት ትኩረት ከተሰጠባቸው ዘርፎች መካከል የሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ተማሪዎች በንድፈ-ሀሳብ የቀሰሙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ችግር ፈቺ ፈጠራዎችን እንዲያቀርቡ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። በትምህርት ቤቶች የኤሌክትሮኒክ ትምህርት (ኢ-ስኩል) ለማጠናከር የሚያስችል የመሰረተ-ልማት ዝርጋታ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። የተማሪዎችን የሳይንስ ምርምር ሥራ ማስተዋወቅ የሚጀመረው በቤተ-ሙከራና በትምህርት ማበልጸጊያ ማዕከላት በመሆኑ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ትምህርት ቤቶች ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት በይፋ የተከፈተው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ አውደ-ርዕይ መልካም ጅማሮ መሆኑን ጠቅሰዋል። በወዳጅነት አደባባይ በዛሬው እለት የተከፈተው ከተማ አቀፍ የተማሪዎችና የመምህራን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ አውደ-ርዕይ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
የ 'ሲቲ ኔት' ቴክኖሎጂ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማት ተግባራዊ ሊደረግ ነው
Jun 6, 2023 122
አዲስ አበባ ግንቦት 29/2015(ኢዜአ)፦ ከ280 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግበት የተገለጸው የ 'ሲቲ ኔት' ቴክኖሎጂ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማት ተግባራዊ መሆን ሊጀምር ነው። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና ኢትዮ- ቴሌኮም ቴክኖሎጂውን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የተፈራረሙት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሰለሞን አማረ እና የቴሌኮም ኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ናቸው። የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትን ተግባራዊ በማድረግ የመዲናዋ ነዋሪዎች በከተማ አስተዳደሩ ስር ባሉ ተቋማት ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ስምምነቱ መፈረሙን አቶ ሰለሞን ገልጸዋል። ለዚህም በየተቋማቱ የኔትወርክ መሰረተ ልማቶች ዝርጋታ እና መተግበሪያዎች የማበልጸግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ቴክኖሎጂው ከፍተኛ ፍጥነት ያለው መሰረተ ልማት በመሆኑም ተቋማቱ አገልግሎታቸውን ለማዘመንና ቀልጣፋ ለማድረግ እንደሚረዳቸው ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ በመዲናዋ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች ስር በሚገኙ 58 ተቋማት እና በ120 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ ይደረጋል። ከ280 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚደረግበት ፕሮጀክት በአራት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው አቶ ሰለሞን የጠቆሙት። 'ሲቲ ኔት' ቴክኖሎጂ የከተማዋን ግብር አሰባሰብ፣ የወሳኝ ኩነት ምዝገባን ጨምሮ የቅሬታና አቤቱታ አቀራረብ ስርዓቶችን ለማዘመን የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ መዲናዋን የሚመጥን ዘመናዊ የሆኑ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎች እንዲኖሩ የሚያስችል ነው ብለዋል። ይኸው ፕሮጀክት በመዲናዋ የስማርት ሲቲ መርሐ-ግብርን እውን ለማድረግ ከተያዙት እቅዶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል። ስምምነቱ በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ የተለያዩ ቢሮዎች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከዋናው የዳታ ማዕከል ጋር በቀላሉ ለማስተሳሰር የሚያስችል ቴክኖሎጂን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ ተመሳሳይ አገልግሎቶችን በአንድ ጊዜ በማከናወንና የአሰራር ስርአትን በማዘመን አስተማማኝ፣ ቀልጣፋ እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ያግዛል ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ።
ስፖርት
የዓለም አይኖች ሁሉ ወደ ኢስታንቡል
Jun 10, 2023 148
የዓለም አይኖች ሁሉ ወደ ኢስታንቡል አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ):- የአውሮፓ እግር ኳስ ትልቁ ክብር ወደ እንግሊዝ ወይስ ወደ ጣልያን ያመራ ይሆን? ማንችስተር ሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን በእጁ ያስገባል? ወይስ ኢንተር ሚላን ለአራተኛ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት ይሆናል? ፔፔ ጋርዲዮላ ወይስ ሲሞኒ ኢንዛጊ? ኧርሊንግ ሃላንድ ወይስ ላውታሮ ማርቲኔዝ? ከአምበሎቹ ኢልካይ ጉንዶጋን እና ሳሚር ሃንዳኖቪች ዋንጫዋን ማን ከፍ ያደርጋል? 75 ሺህ 145 ተመልካች በሚያስተናግደው አታቱርክ ኦሊምፒክ ስታዲየም ከምሽቱ 4 ሰአት በማንችስተር ሲቲ እና ኢንተር ሚላን መካከል የሚደረገው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ለነዚህ ጥያቄዎች ሁሉ ምላሽ ይሰጣል። የዋንጫው አሸናፊ ለሆነው ቡድን የ20 ሚሊዮን ዩሮ ሽልማት ይበረከትለታል። ተጠባቂው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ የዓለምን የእግር ኳስ ቤተሰብ ለ90 ደቂቃ ከዛም ካለፈ ለ120 ደቂቃ ምናልባትም ከዛ በላይ ቀልብ እና ስሜት ይዞ ይቆያል። የእንግሊዙ ማንችስተር ሲቲ ዛሬ የሚጫወተው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለመጀመሪያ ጊዜ ለማንሳት ብቻ ሳይሆን በዓመቱ የሶስትዮሽ ዋንጫ ባለቤትነት ሕልሙን ለማሳካት ነው። ሰማያዊዎቹ በዘንድሮው የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን አንስተዋል። የፔፕ ጋርዲዮላው ማንችስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈ በክለቡ ታሪክ ውስጥ ትልቁን እና ደጋፊዎቹ ለዓመታት የጓጉለትን ስኬት ማስመዝገብ ይችላል። “የእግር ኳስ ሊቅ” እየተባለ የሚጠራው የ52 ዓመቱ ስፔናዊ አሰልጣኝ ዋንጫውን ካነሳ “የዓለማችን የምንጊዜም ምርጥ አሰልጣኞች” ዝርዝር ውስጥ ስሙን ማጻፍ ይችላል እያሉ ነው የእግር ኳስ ባለሙያዎቹ። ጋርዲዮላ የስፔኑ ኃያል ክለብ ባርሴሎና አሰልጣኝ በነበረበት ወቅት ሁለት ጊዜ (እ.አ.አ 2008/09 እና 2010/11) የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አንስቷል። ማንችስተር ሲቲን ይዞ እ.አ.አ 2020/21 የሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ቢደርስም በቼልሲ 1 ለ 0 መሸነፉ የሚታወስ ነው። ማንችስተር ሲቲ በግማሽ ፍጻሜ የ14 ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው ሪያል ማድሪድን በደርሶ መልስ 5 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ደርሷል። ሲቲ በኢትሃድ ስታዲይም በተካሄደው የመልስ ጨዋታ ከጨዋታ ብልጫ ጋር 4 ለ 0 ያሸነፈበት ብቃት አድናቆትን ያስቸረው ነው። ያስመዘገበው ድል ዋንጫውን ያነሳል የሚል ግምትም አሰጥቶታል። ማንችስተር ሲቲ በ2022/23 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር እስካሁን ባደረጋቸው 12 ጨዋታዎች 31 ግቦችን ሲያስቆጥር 5 ግቦችን አስተናግዷል። ካደረጋቸው ጨዋታዎች መካከል በሰባቱ ግብ አላስተናገደም። በመጀመሪያው የውድድር ዓመት አስደናቂ ብቃት እያሳየ የሚገኘው የ22 ዓመቱ ኖርዌያዊ ኮከብ ኧርሊንግ ሃላንድ በሻምፒዮንስ ሊጉ በ10 ጨዋታዎች 12 ግቦችን በማስቆጠር የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን እየመራ ነው። ወጣቱ አጥቂ በውድድር ዓመቱ በአጠቃላይ 52 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። በማንችስተር ሲቲ የመጀመሪያውን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ የማንሳት መንገድ ላይ የጣልያኑ አንጋፋ እና ኃያል ክለብ ኢንተር ሚላን ቆሟል። በ47 ዓመቱ የጣልያን የቀድሞ ኮከብ አጥቂ ሲሞኒ ኢንዛጊ የሚሰለጥነው ኢንተር ሚላን በተመሳሳይ እንደ ማንችስተር ሲቲ በውድድር ዓመቱ ሶስተኛ ዋንጫውን ለማንሳት ይጫወታል። ኔራዙሪዎቹ(ጥቁር እና ሰማያዊዎቹ) በዘንድሮው የውድድር ዓመት የጣልያን ጥሎ ማለፍ እና የጣልያን አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫን አንስተዋል። ኢንተር ሚላን ለአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ የደረሰው የከተማ ተቀናቃኙን ኤሲ ሚላንን በግማሽ ፍጻሜው በደርሶ መልስ 3 ለ 0 በማሸነፍ ነው። የጣልያኑ ክለብ በዘንድሮው ዓመት የሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር 12 ጨዋታዎችን አድርጎ 19 ግቦችን ሲያስቆጥር 10 ጎሎችን አስተናግዷል። አርጀንቲናዊው አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ እና ቤልጂየሚዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሮሜሎ ሉካኩ እንዲሁም የአማካይ ተጫዋቹ ኒኮሎ ባሬላ በሻምፒዮንስ ሊጉ በተመሳሳይ ሶስት ግቦችን ለኢንተር ሚላን አስቆጥረዋል። ላውታሮ ማርቲኔዝ በጣልያን ሴሪ አ 21 ግቦችን በማስቆጠር ናይጄሪያዊውን የናፖሊ አጥቂ ቪክቶር ኦሲሜን ተከትሎ በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። አጠቃላይ በውድድር ዓመቱ 28 ግቦችን አስቆጥሯል። ኢንተር ሚላን ከዚህ ቀደም የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሶስት ጊዜ አንስቷል። (እ.አ.አ 1964፣ 1965 እና 2010) ኢንተር ሚላን እ.አ.አ በ2010 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ የደረሰው በግማሽ ፍጻሜው በወቅቱ በአሰልጣኝ ፔፔ ጋርዲዮላ ይመራ የነበረውን ባርሴሎናን በደርሶ መልስ ውጤት 3 ለ 2 በማሸነፍ ነበር። በወቅቱ የኢንር ሚላን አሰልጣኝ የነበሩት ፖርቹጋላዊ አሰልጣኝ ጆዜ ሞውሪኒዮ ናቸው። ማንችስተር ሲቲ እና ኢንተር ሚላን ከዚህ ቀደም በፉክክር ጨዋታዎች ላይ ተገናኝተው አያውቁም። ከዚህ በፊት ሁለት ጊዜ የወዳጅነት ጨዋታ አድርገው አንድ አንድ ጊዜ ተሸናንፈዋል። (እ.አ.አ 2010 ኢንተር ሚላን እና እ.አ.አ 2011 ማንችስተር ሲቲ በተመሳሳይ 3 ለ 0 አሸንፈዋል) የ42 ዓመቱ ፖላንዳዊ ዳኛ ሲሞን ማርሲኒያክ የተጠባቂው ጨዋታ የመሐል ሜዳ አለቃ ናቸው። የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፈው ክለብ ከዋንጫው በተጨማሪ የ20 ሚሊዮን ዩሮ ሽልማት ሲያገኝ ተሸናፊው ክለብ 15 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ሽልማት ይበረከትለታል። የዓለም አይኖች ዛሬ ከምሽቱ 4 ሰአት ጀምሮ በአታቱርክ ኦሊምፒክ ስታዲየም ላይ ያርፋሉ።
የዋንጫ ተፎካካሪዎቹ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ባህር ዳር ከተማ ተጠባቂውን ጨዋታ ዛሬ ያደርጋሉ
Jun 10, 2023 45
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሐ-ግብር የፕሪሚየር ሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ተከታዩ ባህር ዳር ከተማ የሚያደርጉት ጨዋታ በእግር ኳስ አፍቃሪው በኩል በጉጉት ይጠበቃል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከቀኑ 10 ሰአት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይካሄዳል። ጨዋታው በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ግንቦት 18/2015 መካሄድ የነበረበት ቢሆንም በከባድ ዝናብ ምክንያት ሜዳው ማጫወት ባለመቻሉ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሞ የቆየ ነው። የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የውድድር እና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ጨዋታው በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስታዲየም እንዲደረግ መወሰኑ ይታወቃል። በዚሁ መሰረት የሁለቱ ክለቦች ወሳኝ ጨዋታ ዛሬ ይከናወናል። በደረጃ ሰንጠረዡ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ58 ነጥብ 1ኛ ሲሆን ባህር ዳር ከተማ በ53 ነጥብ 2ኛ ደረጃን ይዟል። በአሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ የሚሰለጥነው ቅዱስ ጊዮርጊስ እስከ አሁን በፕሪሚየር ሊጉ ካደረጋቸው 26 ጨዋታዎች 17ቱን ሲያሸንፍ 2 ጊዜ ተሸንፎ፤ 7 ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይቷል። በ26ቱ ጨዋታዎች ፈረሰኞቹ 48 ግብ ሲያስቆጥሩ 17 ጎሎችን አስተናግደዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት አምስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች በሶስቱ አሸንፎ በአንድ ተሸንፎ አንድ ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይቷል። በአሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛው የሚመራው ባህር ዳር ከተማ በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው 26 ጨዋታዎች 15ቱን ሲያሸንፍ በሶስቱ ተሸንፎ፤ በ8ቱ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። የጣና ሞገዶቹ በ26ቱ ጨዋታዎች 47 ጎሎችን ሲያስቆጥሩ 24 ግቦችን አስተናግደዋል። ባህር ዳር ከተማ ካለፉት አምስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ሶስቱን አሸንፎ አንዱን ተሸንፎ አንድ ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥቷል። ቅዱስ ጊዮርጊስ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈ ከተከታዩ ባህር ዳር ከተማ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ስምንት ከፍ በማድረግ 16ኛውን የፕሪሚየር ሊጉ ዋንጫ ለማንሳት ይበልጥ ይቃረባል። በአንጻሩ ባህር ዳር ከተማ በዋንጫ ፉክክሩ ለመቆየት የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ የሚጠበቅበት ሲሆን ጨዋታውን ካሸነፈ ከፈረሰኞቹ ጋር ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ያደርጋል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያ ዙር በ10ኛ ሳምንት በድሬዳዋ ስታዲየም ያደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ የሚታወስ ነው። በተስተካካይ ጨዋታው ምክንያት በ28ኛ ሳምንት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና እንዲሁም ባህር ዳር ከተማ ከሲዳማ ቡና ሊያደርጓቸው የነበሩ ጨዋታዎች ሰኔ 18 2015 እንደሚከናወኑ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር እና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ አስታውቋል።
ቁመተ መለሎው አትሌት የተናገረውን በተግባር ፈጽሟል
Jun 10, 2023 99
“የዓለም ክብረ ወሰን መስበሬ አላስገረምኝም ምክንያቱም ክብረ ወሰኑን እንደማሻሽለው አውቅ ነበር” አትሌት ለሜቻ ግርማ ወጣቱ አትሌት 19 ዓመት ያልተደፈረውን ክብረ ወሰን ሰባብሮታል። ማይክሮ ሰኮንድ አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ):- የዓለም አትሌቲክስ ትናንት በፓሪስ ሰባስቲያን ቻርሌቲ ስታዲየም የተደረገውን የዳይመንት ሊግ ውድድር “አስደናቂ እና የእብደት ምሽት” ሲል ገልጾታል። በውድድሩ ሶስት የዓለም ክብረ ወሰኖች ተሰባብረዋል። በዓለም አትሌቲክስ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድሮች ስማቸው ቀድሞ ከሚነሱ ተወዳዳሪዎች ይገኝበታል። ከልጅነቱ ጀምሮ ባለው ቁመት እና ቁመና ጥሪ እና መክሊቱ አትሌቲክስ ነው ያሉ ብዙዎች ናቸው። 3 ሺህ ሜትር መሰናክልን በተደጋጋሚ ጊዜ ከስምንት ደቂቃ በታች በመግባት የሚስተካከለው የለም። በኦሊምፒክ እና በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በርቀቱ የብር ሜዳሊያዎችን አግኝቷል። ባለ ረጅም ቅልጥሙ አትሌት በውድድር ያለውን የእግር አጣጣል እና የአጨራረስ ብቃት ከብዙ የአትሌቲክስ ተንታኞች ውዳሴን አምጥቶለታል። የዓለም አትሌቲክስ “እያበበ ያለው ወጣቱ ኮከብ” ሲል ይገልጸዋል። በዓለም አትሌቲክስ የዓለም ምርጥ ወጣት አትሌት ሽልማት እጩዎች ውስጥ ገብቶ ያውቃል። የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን የአፍሪካ ወጣት ምርት አትሌት ሽልማት አሸናፊም ነው። የኬንያውያን የ”ባህል ስፖርት” ነው በሚባለው የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል የኬንያ አትሌቶችን በማሸነፍ ውድድሩ የአንድ አገር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያም መሆኑን አስመስክሯል። የዓለም የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር ክብረ ወሰን ባለቤት ነው። እያወራን ያለነው ከአሰላ ስለ ተገኘው እና 1 ሜትር ከ 85 ስለሚረዝመው የ22 ዓመቱ ቁመተ መለሎ አትሌት ለሜቻ ግርማ ነው። ትናንት በፓሪስ የዘንድሮው ዓመት የአራተኛ ዙር የዳይመንድ ሊግ ውድድር ተካሄዷል። በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር አትሌት ለሜቻ ግርማ 7 ደቂቃ ከ52 ሴኮንድ ከ11 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት ለ19 ዓመታት በኳታሪው አትሌት ሳይፍ ሰኢድ ሻሂን ተይዞ የነበረውን የርቀቱን ክብረ ወሰን በ1 ሴኮንድ ከ52 ማይክሮ ሴኮንድ አሻሽሎታል። አትሌት ለሜቻ በመጨረሻው ዙር ብቻውን ተነጥሎ በመውጣት እና ፍጥነቱን በመጨመር ያሳየው አጨራረስ አስደናቂ የሚባል ነበር። አትሌቱ ከውድድሩ በፊት የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ክብረ ወሰንን ለመስበር እንደሚሮጥ ገልጾ ነበር። አትሌት ለሜቻ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ክብረ ወሰን የመስበር የሁልጊዜ ሕልሙን አሳክቷል ። “በማሸነፌ በጣም ደስተኛ ነኝ” ሲል አትሌት ለሜቻ ከውድድሩ በኋላ ለዓለም አትሌቲክስ በሰጠው አስተያየት ገልጿል። “ዓመቱን የጀመርኩት የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ክብረ ወሰን በመስበር ነው፤ በጣም ደስ ብሎኛል ኮርቻለሁ ደስ ብሎኛል” ብሏል። “በውድድሩ በጣም በፍጥነት ስሮጥ እንደነበር ተሰምቶኛል በራስ መተማመን ላይ ነበርኩኝ፤ የዓለም ክብረ ወሰኑ አላስገረመኝም በፓሪስ እንደማሻሽለው አቅጄ ነበር ድሉ የሙሉ ቆራጥነት ውጤት ነው” ያለው አትሌት ለሜቻ። እንደተለመደው የአትሌቴ ክብረ ወሰን በዓለም አትሌቲክስ ክብረ ወሰንን አጣርቶ የማጽደቅ ሂደት ውስጥ ያልፋል። አትሌቱ የክብረ ወሰኑ ባለቤት መሆኑ የሚረጋገጠው የዓለም አትሌተክስ የገባበትን ሰአት አጣርቶ ሲያጸድቅ ነው። በውድድሩ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት አብርሃም ስሜ አራተኛ ወጥቷል። ትናንት በ5 ሺህ ሜትር ሴቶች በተደረገው ውድድር ኬንያዊቷ አትሌት ፌይዝ ኪፕዬጎን 14 ደቂቃ ከ5 ሴኮንድ ከ20 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት በኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ ላለፈው ሶስት ዓመት ተይዞ የነበረውን የርቀቱን የዓለም ክብረ ወሰን በ 1 ሴኮንድ ከ42 አሻሽላለች። በውድድሩ ኬንያዊቷ አትሌት ከኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ ጋር እልህ አስጨራሽ ፉክክር አድርጋለች። አትሌት ለተሰንበት 14 ደቂቃ ከ 7 ሴኮንድ ከ94 ሴኮንድ በመግባት ሁለተኛ ወጥታለች። ሌላኛዋ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን አጠናቃለች። ኬንያዊቷ አትሌት ፌይዝ ኪፕዬጎን ባለፈው ሳምንት በጣልያን ፍሎረንስ ከተማ በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች ውድድር 3 ደቂቃ ከ49 ሴኮንድ ከ11 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት በአትሌት ገንዘቤ ዲባባ ተይዞ የነበረውን የርቀቱን የዓለም ክብረ ወሰን በአንድ ሴኮንድ ማሻሻሏ የሚታወስ ነው። አትሌቷ በስምንት ቀናት ውስጥ ሁለት የዓለም ክብረ ወሰን በመስበር አዲስ ታሪክ ጽፋለች። በ2 ማይል የወንዶች ውድድር የ22 ዓመቱ ኖርዌያዊ አትሌት ጃኮብ ኢንግብሪግስተን 7 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ ከ10 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት የርቀቱን የዓለም ክብረ ወሰን ሰብሯል። በፓሪስ የተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ሶስት የዓለም ክብረ ወሰኖች የተሰበሩበት ታሪካዊ ምሽት ሆኖ አልፏል። የዘንድሮው አምስተኛው ዙር የዳይመንድ ሊግ ውድድር ሰኔ 8 2015 በኖርዌይ ኦስሎ ይካሄዳል።
በፕሪሚየር ሊጉ 28ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
Jun 9, 2023 68
አዲስ አበባ ሰኔ 2/2015(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ28ኛ ሳምንት ሁለተኛ ቀን ውሎ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋሉ። አዳማ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና ከቀኑ ዘጠኝ ሰአት ላይ ይጫወታሉ። በደረጃ ሰንጠረዡ አዳማ ከተማ በ36 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሀዲያ ሆሳዕና በ39 ነጥብ 4ኛ ደረጃን ይዟል። አዳማ ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች በአንዱ ሲያሸንፍ፤ በሁለቱ ተሸንፎ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው ሀዲያ ሆሳዕና ካለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ሁለቱን አሸንፎ፤ በአንዱ ሲሸነፍ በአንዱ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያ ዙር ያደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወሳል። በሌላኛው የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ28ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክን ከሃዋሳ ከተማ ከምሽቱ 12 ሰአት ያገናኛል። ከሊጉ አስቀድሞ መውረዱን ያረጋገጠው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ12 ነጥብ የመጨረሻውን 16ኛ ደረጃ የያዘ ሲሆን ሃዋሳ ከተማ በ38 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች በአራቱ ሲሸነፍ አንድ ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ በበኩሉ ካለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች አንዱን ሲያሸንፍ አራት ጊዜ አቻ ወጥቷል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ትናንት በተደረጉ የ28ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 1 እንዲሁም አርባ ምንጭ ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲን 2 ለ 1 ማሸነፋቸው ይታወቃል።
አካባቢ ጥበቃ
በረሃማነትን ለመከላከል ዓለም አቀፍ ትብብር ያስፈልጋል-ዶክተር እንድርያስ ጌታ
Jun 10, 2023 44
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ):- በረሃማነትን ለመከላከል ዓለም አቀፍ ትብብር አስፈላጊ መሆኑን የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንድርያስ ጌታ ገለጹ። 29ኛውን የዓለም በረሃማነትን የመከላከል ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀው ሶስተኛው ዓለም አቀፍ ጉባኤ ትናንት በቻይና ተጀምሯል። ጉባኤው በቻይና የሳይንስ አካዳሚ እና በአካዳሚው ሺንጂያንግ የኢኮሎጂ እና ጂኦግራፊ ኢንስቲትዩት አጋርነት የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንድርያስ ጌታ የተመራ ልዑክ በጉባኤው ላይ እየተሳተፈ ነው። ሚኒስትር ዴኤታው በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር በረሃማነትን ለመከላከል ዓለም አቀፍ ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል። ዶክተር እንድርያስ በጉባኤው በኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢዎች በረሃማነትን ለመከላከል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ተሞክሮ አቅርበዋል። ከፎረሙ ጎን ለጎን የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር በቻይና የሳይንስ አካዳሚ እና ሺንጂያንግ የኢኮሎጂ እና ጂኦግራፊ ኢንስቲትዩት በኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢዎች በረሃማነትን መከላከል የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት እንደሚፈራረሙ ተገልጿል። ዶክተር እንድሪያስ ከሲኖ አፍሪካ የጋራ ምርምር ማዕከል ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ይወያያሉ ተብሎም ይጠበቃል። እስከ ሰኔ 15/2015 በሚቆየው ዓለም አቀፍ ፎረም ላይ የተለያዩ አገራት በረሃማነትን በመከላከል ረገድ ያላቸውን ተሞክሮዎች እንደሚያቀርቡ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መረጃ አመልክቷል። በተጨማሪም የተለያዩ አገራት ባለሙያዎች፣ ተመራማሪዎች እና ልዑካን ቻይና በረሃማነትን ለመከላከል በ “Takilmakan” በረሃ እያከናወነች ያለውን ስራ እንደሚጎበኙም ተገልጿል።
በመጀመሪያው አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተገኙ ስኬቶችን በሁለተኛው ምዕራፍ መድገም ይገባል--የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Jun 10, 2023 37
አዲስ አበባ ሰኔ 3/2015(ኢዜአ)፦ በመጀመሪያው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተገኙ ስኬቶችን በሁለተኛው ምዕራፍ ለመድገም መረባረብ ይገባል ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። በቀጣዮቹ የክረምት ወራት የትምህርት ተቋማትን ለመማር ማስተማር ምቹ የማድረግ ስራ እንደሚሰራም አገልግሎቱ ገልጿል። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በተለያዩ ወቅታዊ አገራዊ ጉዳዩች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በመጀመሪያው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተገኙ ስኬቶችን በሁለተኛው ምዕራፍ መድገም ይገባል ብለዋል። በመጀመሪያው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ25 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ለሶስት ዓመታት በሚተገበረው የሁለተኛው ምዕራፍ መርሃ ግብርም 25 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል። ለዚህ ስኬትም ህዝቡ በመጀመሪያው ምዕራፍ ያሳየውን ርብርብ በተጠናከረ መልኩ መድገም ይገባዋል ብለዋል። በተያያዘም በክረምቱ ወራት የትምህርት ተቋማትን ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ የማድረግ ስራ እንደሚሰራም ገልጸዋል። ንቅናቄው በቅርቡ ይፋ የሚደረግ መሆኑን ጠቁመው፤ ለንቅናቄው ስኬታማ መሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሊረባረቡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። በክረምቱ ወራት በሚከናወነው የመኸር እርሻ አንድም መሬት ጦም እንዳያድር በመሰራት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። በከተሞች አካባቢ የከተማ ግብርናን ማስፋት እንደሚገባም ገልጸዋል። የሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ በአፋር ክልል መጀመሩ ይታወቃል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የኢትዮጵያን የውሃ ሀብቶችን ለመጠበቅ ጉልህ ፋይዳ ያለው ነው- የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር
Jun 9, 2023 62
አርባ ምንጭ ሰኔ 2/2015 (ኢዜአ):- የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ኢትዮጵያን የውሃ ሀብቶቿን እንድትጠብቅ እና እንድታቆይ ወሳኝ አበርክቶ እንዳለው የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። 21ኛው ዓለም አቀፍ የውሃ አውደ ጥናት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው፡፡ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቶቿን ጥቅም በዘላቂነት ለማረጋገጥ የ10 ዓመት እቅድ ነድፋ ተግባራዊ እያደረገች ነው። የውሃ ሀብቶችን በተቀናጀ ሁኔታ ለማስተዳደር፣ ውሃን ለመጠጥና ለኃይል አቅርቦት እንዲውል ማድረግ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል እንደሚገኙበት ገልጸዋል። "ውሃ ሕይወት እንደመሆኑ መጠን አስቀድመን ለውሃው ሕይወት በመስጠት ማቆየት ይገባል" ያሉት ሚኒስትር ዲኤታው የውሃ ሀብቶቻችን ጥቅም ዘላቂ ለማድረግ የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ መጠበቅ እንደሚገባ አመልክተዋል። በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የውሃ ሀብቶችን ከመጠበቅ አኳያ ትልቅ ፋይዳ አለው ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው። መርሐ-ግብሩ ለግብርና፣ኢንዱስትሪ፣ቱሪዝም፣መዝናኛ፣መጠጥ ብቻ ሳይሆን ለአገር ልማት ወሳኝ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። መንግስት ለውሃ ሀብት ልዩ ጥበቃ እና እንክብካቤ ትኩረት በመስጠት በተቀናጀ መንገድ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንትፊክ ዳይሬክተር ዶክተር ቦጋለ ገብረማርያም በበኩላቸው ከውሃ ሀብት ዘርፍ ዘላቂ ጥቅም ለማግኘት የተፋሰስ አካላት እንክብካቤና ልማት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። "በዘርፉ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኩል የተደረጉ ምርምሮች መደርደሪያ ላይ ከመቀመጥ አልፈው አስፈላጊው ጥቅም ላይ እንዲውል ትኩረት ያስፈልጋል" ብለዋል። የካናዳ 'ኤምሲማስተር' ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ፖላን ኩሊባሊ ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ አሻራ ልማት የውሃ ሀብት አቅምን ከማሳደግም በላይ ለኢትዮጵያ እድገት ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። እንደ ኢትዮጵያ ያሉ አገራት የኃይል አቅርቦት በእጅጉ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ የውሃ ሀብትን መጠበቅና በአግባቡ መጠቀም ወሳኝ እንደሆነ ገልጸዋል። 21ኛው ዓለም አቀፍ የውሃ አውደ ጥናት እስከ ነገ ይቆያል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለአረንጓዴ አሻራ ልማት 55 ሚሊየን ችግኝ መዘጋጀቱን የግብርና ቢሮ አስታወቀ
Jun 9, 2023 55
አሶሳ ሰኔ 2 /2015 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ ልማት የሚውል 55 ሚሊየን ችግኝ መዘጋጀቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሃላፊ አቶ ባበክር ከሊፋ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ የተዘጋጀው ችግኝ ባለፈው የበጋ ወቅት የአፈርና ውሃ ጥበቃ የተካሄደበት 29 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የሚተከል መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም አብዛኛው የክልሉ ህዝብ ተሳታፊ ለማድረግ መታቀዱን የገለጹት ሀላፊው፤ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የሚካሄድበት ጊዜ በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ገልጸዋል። የሚተከለው ችግኝ የተፈጥሮ ሃብት መልሶ እንዲያገግም የሚያግዝ ከመሆኑም ባሻገር ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ቡና፣ ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ቀርከሃን ጨምሮ ሌሎች ሃገር በቀል ችግኞች እንደሚገኙበት አመልክተዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፈው ዓመት ክረምት ከተተከለው 42 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኝ ውስጥ ከ90 በመቶ በላይ መጽደቁን አቶ ባበክር አስታውሰዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ብዝሃ ቋንቋ በማጎልበት ረገድ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል - የኮሚሽኑ ተጠባባቂ ዋና ጸሀፊ
Jun 6, 2023 149
አዲስ አበባ ግንቦት 29/2015(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ብዝሃ ቋንቋ በማጎልበት ረገድ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የኮሚሽኑ ተጠባባቂ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ፔድሮ ተናገሩ። የሩስያ ቋንቋ ዓለም አቀፍ ቀን የመንግሥታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ተጠባባቂ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ፔድሮ እና በኢትዮጵያ የሩስያ ፌደሬሽን አምባሳደር ይቭጌኒ ተርክሂን ጨምሮ በርካታ እንግዶች በተገኙበት በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ተከብሯል። የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ተጠባባቂ ዋና ስራ ጸሀፊ አንቶኒዮ ፔድሮ፤ የቋንቋ ቀን ከሰው ልጆች ባህል፣ ሥልጣኔ፣ ሰብዓዊነትና ሉዓላዊነት ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሥራ ቋንቋ የሆነው የሩስያ ቋንቋ ቀን በመላው ዓለም ባሉ የመንግስታቱ ድርጅት ቢሮዎች እንደሚከበርም ገልጸዋል፡፡ የሩስያ ቋንቋ ቀን የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት ተብሎ ከሚወደሰውና አፍሪካዊ ማንነት ከሚጋራው ዕውቁ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ጋር በማስተሳሰር የሚከበር ቀን መሆኑም ገልፀዋል። ከ350 ሚሊየን በላይ ተናጋሪዎች ያሉት ሩስያኛ ቋንቋ በተለይም ምስራቅ አውሮፓና ማዕከላዊ ኤስያ ቀጣና በስፋት የሚነገር መሆኑን ገልጸዋል። በትርጉም ቋንቋነቱ በዓለም አራተኛ እንዲሁም በኢንተርኔት መረጃ ምንጭነቱ በዓለም ላይ ሁለተኛ ደረጃ እንደሚይዝ ገልጸው፤ ይህም ለመንግስታቱ ድርጅት የስራ ቋንቋ እንዲሆን አስችሎታል ነው ያሉት። በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ለብዝሃ ቋንቋ ዕድገት ከአጋር አካላት ጋር በጋራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በኮሚሽኑ ቤተ መፃሕፍት የአሌክሳንደር ፑሽኪን ክፍል መደራጀቱንና በቋንቋ ማዕከሉ የሩስያ ቋንቋ ትምህርት ለመስጠት ከአዲስ አበባ ከሚገኘው የሩስያ ሳይንስና ቋንቋ ማዕከል ጋር በትብብር እንደሚሰራም ገልፀዋል። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተርክሂን፤ ዕለቱ ብዝሃ ቋንቋና ብዝሃ ባህልን ለማስፋፋት እንደሚከበር ገልጸው፤ የቋንቋ ቀን ሲከበርም ከሰው ልጆች ማንነት፣ ሥልጣኔዎችና ቅርሶች ዐውድ አንፃር የሚታይ መሆኑን ተናግረዋል። በአንዳንድ አካላት ቋንቋን ፖለቲካዊ መልክ የማስያዝ አካሄዶች መኖራቸውን ጠቅሰው ሩስያኛ ቋንቋም በአንዳንድ የአውሮፓ አገራት ችግሮች የገጠሙት መሆኑን ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቀኑን እንዲከበር በማድረጉ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የሩስያ ቋንቋና ዕውቀትን ለኢትዮጵያዊያንና በኢትዮጵያ ለሚኖሩ የሌሎች አገራት ዜጎች ለማስፋፋትም በአዲስ አበባ የፑሽኪን የሳይንስና ባህል ማዕከል እየተሰራ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል። በአፍሪካ ደረጃ የሩስያ ቋንቋን ለማስተዋወቅም ከሀገራት ጋር በኢኮኖሚ፣ በትምህርትና ቋንቋ እንዲሁም በቱሪዝም መስኮች ሁሉን አቀፍ ትብብሮች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በአውሮፓውያኑ 2010 የሩሲያ ቋንቋ በየዓመቱ እንዲከበር ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ በአዲስ አበባ በሚገኘው የኮሚሽኑ አዳራሽ በየዓመቱ ይከበራል። የመንግሥታቱ ደርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ደግሞ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2018 ጀምሮ ቀኑን በተለያዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ቀጥሏል።
ኢትዮጵያ ከተባበሩት መንግስታት ዩኤን ሀቢታት መርሃ-ግብር ጋር ያላትን ትብብር እና አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ ነች--የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር
Jun 6, 2023 109
አዲስ አበባ ግንቦት 29/2015(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት ከተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ሰፈራ መርሃ-ግብር (UN-Habitat) ጋር ያለውን ትብብር እና አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ። "ለተሻለ የከተማ ዕድገት!" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኘውን ጉባኤ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በይፋ ከፍተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልዑክ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ በሚገኘው ሁለተኛው የዩ ኤን ሃቢታት ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ የልዑኩ መሪ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን በመድረኩ ኢትዮጵያ በዘርፉ እያከናወነች ያለችውን ተግባራት በተመለከተ ማብራሪያ አቅርበዋል። ሚኒስትር ዴኤታው በንግግራቸው የኢትዮጵያ መንግስት በከተማ ሴክተር እያከናወናቸው ያሉ ዋና ዋና የፖሊሲ መዋቅራዊ ለውጦችን ገልጸዋል። አዲሱ የከተማ አጀንዳ እና የልማት ግቦችን በከተሞች ዘርፍ በተሻለ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ የኢትዮጵያ መንግስት ከዩ ኤን ሃቢታት ጋር ያለውን ትብብር እና አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑንም አስታውቀዋል። ጉባኤው እስከ ሰኔ 2/2015 ዓ.ም ድረስ እንደሚቀጥል ከከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
የሩስያ ቋንቋ ዓለም አቀፍ ቀን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ተከበረ
Jun 6, 2023 112
አዲስ አበባ ግንቦት 29/2015(ኢዜአ):- የሩስያ ቋንቋ ዓለም አቀፍ ቀን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ተከበረ። የመንግሥታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ተጠባባቂ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ፔድሮ እና በኢትዮጵያ የሩስያ ፌደሬሽን አምባሳደር ኢቭጌኒ ተርክሂን ጨምሮ በርካታ እንግዶች በክብረ በዓሉ ላይ ተገኝተዋል። የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ተጠባባቂ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ፔድሮ፤ የቋንቋ ቀን ከሰው ልጆች ባህል፣ ሥልጣኔ፣ ሰብዓዊነትና ሉዓላዊነት ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሥራ ቋንቋ የሆነው የሩስያ ቋንቋ ቀን በመላው ዓለም ባሉ የመንግስታቱ ድርጅት ቢሮዎች እንደሚከበርም ገልጸዋል፡፡ የሩስያ ቋንቋ ቀን የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት ተብሎ ከሚወደሰውና አፍሪካዊ ማንነት ከሚጋራው ዕውቁ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ጋር በማስተሳሰር የሚከበር ቀን መሆኑም ገልፀዋል። ከ350 ሚሊየን በላይ ተናጋሪዎች ያሉት ሩስያኛ ቋንቋ በተለይም በማዕከላዊና ምስራቅ አውሮፓ ቀጣና በስፋት እንደሚነገር ጠቁመዋል። በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የአሌክሳንደር ፑሽኪን ክፍል መደራጀቱንና በቋንቋ ማዕከሉ የሩስያ ቋንቋ ትምህርት እንደሚሰጥ ተናግረዋል። ሩስያ ቋንቋ የሩስያዊያንን ሥልጣኔ፣ ባህልና ሥነ-ጽሁፍን ያቀፈ መሆኑን ገልጸው፤ ኮሚሽኑ ለብዝሃ ቋንቋ ዕድገት ከአጋር አካላት ጋር በጋራ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በቀጣይም የሩስያ ቋንቋ ለመማር ፍላጎት ያላቸው ሰራተኞች ሁሉ ለማስተማር በአዲስ አበባ ከሚገኘው የሩስያ ሳይንስና ቋንቋ ማዕከል ጋር በትብብር እንደሚሰራም ገልፀዋል። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተርክሂን፤ ዕለቱ ብዝሃ ቋንቋና ብዝሃ ባህልን ለማስፋፋት እንደሚከበር ገልጸው፤ የቋንቋ ቀን ሲከበርም ከሰው ልጆች ማንነት፣ ሥልጣኔዎችና ቅርሶች ዐውድ አንፃር የሚታይ መሆኑን ተናግረዋል። በአንዳንድ አካላት ቋንቋን ፖለቲካዊ መልክ የማስያዝ አካሄዶች መኖራቸውን ጠቅሰው ሩስያኛ ቋንቋም በአንዳንድ የአውሮፓ አገራት ችግሮች የገጠሙት መሆኑን ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቀኑን እንዲከበር በማድረጉ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የሩስያ ቋንቋና ዕውቀትን ለኢትዮጵያዊያንና በኢትዮጵያ ለሚኖሩ የሌሎች አገራት ዜጎች ለማስፋፋትም በአዲስ አበባ የፑሽኪን የሳይንስና ባህል ማዕከል እየተሰራ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል። የመንግሥታቱ ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በአውሮፓውያኑ 2010 የሩሲያ ቋንቋ በየዓመቱ እንዲከበር ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ በአዲስ አበባ በሚገኘው የኮሚሽኑ አዳራሽ በየዓመቱ ይከበራል። የመንግሥታቱ ደርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ደግሞ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2018 ጀምሮ ቀኑን በተለያዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ቀጥሏል።
ፕሬዝዳንት ፑቲን ለአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
May 25, 2023 349
አዲስ አበባ ግንቦት 17/2015 (ኢዜአ)፦የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን ለቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለአሁኑ የአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንከዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ለአፍሪካውያን የድል ምልክት ነው ያሉ ሲሆን የአፍሪካውያን የነጻነት፣የሰላምና የብልጽግና ፍላጎት ማሳያ ነው ብለዋል። ህብረቱ ከተመሰረተበት ግዜ አንስቶ ለብዙ አስርተ ዓመታት በዓለም አቀፍ መድረኮች አፍሪካውያንን በመወከል የባለብዙ ወገን ውይይቶችንና ትብብርን በማጎልበት ትልቅ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት ለችግሮቻቸው በጋራ ምላሽ የሚሰጡበትን መንግድ ያመቻቸ መሆኑን ጠቁመው አህጉራዊ ትብብርን በተለያዩ መስኮች እንዲያጠናከሩም መንገድ ከፍቷል ብለዋል። በዚህም ለአፍሪካ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት የላቀ ሚና ማበርከቱንና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ያላትን ተሳትፎ እንድታሳድግ ህብረቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ሩሲያ ከአፍሪካ አጋሮቿ ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከር ልዩ ትኩረት ትሰጣለች ያሉት ፕሬዝዳንቱ እ.አ.አ በ2019 የተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ -ሩሲያ ጉባኤ በአፍሪካና በሩሲያ መካከል ያሉ ትብብሮች እንዲጠናከሩ አስችሏል ብለዋል። በመጪው ሃምሌ ወር በሩሲያ የሚካሄደው ሁለተኛ የአፍሪካ ሩሲያ ጉባኤም ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር ለሚኖራት ትብብር አዲስ ምዕራፍ እንደሚፈጥር ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ሐተታዎች
አፋጣኝ መፍትሔ የሚያሻው የምርታማነት ፀር
May 27, 2023 336
(ኤልያስ ጅብሪል) አሲዳማ አፈር የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከሰባት በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al+3) ንጥረ- ነገሮች የሚበዙበት አፈር ማለት ነው፡፡ የአፈር አሲዳማነት በሀገራችን በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ የሚገኝ የአፈር ለምነት ችግር ሲሆን፤ ከፍተኛ ዝናብ የሚያገኙና በምርታማነታቸው የተሻሉ ናቸው የሚባሉትን የሀገሪቱን አካባቢዎች ጭምር እየጎዳ መሆኑንም ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት፡፡ የአፈር ጤንነት ችግሮች በሦስት ዋና ዋና መንገዶች ይገለፃሉ፡፡ ይኸውም አሲዳማነት፣ የጨዋማነት ችግር የሚነሳበትና ኮትቻማ/ጥቁር ወይም መረሬ አፈር/ ብሎ ማስቀመጥ እንደሚቻል በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊ ፋኖሴ መኮንን ይናገራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ከ15 ሚሊየን ሄክታር በላይ የሚታረስ መሬት ሲኖር ወደ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በአሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነ ነው የጠቀሱት፡፡ አፈር ሰብሎች የሚፈልጓቸውን ንጥረ-ነገሮች በተሟላና በተመጣጠነ መልኩ ሳይዝ ሲቀር ምርታማነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚወድቅ አቶ ፋኖሴ ይገልጻሉ። ከዚህ አኳያ በኢትዮጵያ ከ1 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጎዳ በመሆኑ ምርታማነቱ ምንም በሚባል ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ይጠቁማሉ። እፅዋት ከአየር፣ ውሃና የፀሐይ ብርሃን በተጨማሪ 18 ዓይነት ንጥረ-ነገሮችን ከአፈር ውስጥ ሊያገኙ እንደሚችሉ ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡ የአፈር አሲዳማነት መንስኤዎች አሲዳማነት በአንድ ጊዜ ተፈጥሮ የሚቆይ ሳይሆን በሂደት እየጨመረ እና እየተስፋፋ የሚሄድ ክስተት ነው፡፡ ለአፈር አሲዳማነት በዋነኝነት የዝናብ መብዛት፣ የአፈር መሸርሸር፣ የሰብል ተረፈ-ምርት ሙሉ በሙሉ ከማሳ ማንሳት እና ፍግ አለመጠቀም፣ እንዲሁም አሲዳማ ዝናብ የመሳሰሉት አፈር ውስጥ ያሉ ለተክሉ እድገት ጠቃሚ ንጥረ-ነገሮች እንዲሟጠጡ እንደሚያደርግ በመንስኤነት ይጠቀሳሉ። የአፈር አሲዳማነት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚስተዋል ሲሆን ለአብነትም አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ተጠቃሾች እንደሆኑ አቶ ፋኖሴ ተናግረዋል፡፡ አሲዳማ አፈርን በኖራ የማከም ዘዴ አሲዳማ አፈርን ለመከላከል በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ መንገዶች ከሚወሰዱ እርምጃዎች ባሻገር አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ በዋናነት የሚጠቀስ መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ አፅንዖት ሰጥተው የተናገሩት፡፡ የተለያዩ አፈርን የማከሚያ ግብአቶች ያሉ ቢሆንም በቀላሉ ከመገኘትና ከዋጋው ርካሽነት አንፃር ካልሽየም ካርቦኔት ወይም “ የግብርና ኖራ" እየተባለ የሚጠራው በስፋት አገልግሎት ላይ እንደሚውል ገልጸዋል፡፡ ወደ 15 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር የሚታረስ መሬት ሲኖር፤ ከዚህ ውስጥ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር ወይም ከ43 በመቶ የማያንሰው በአሲዳማ አፈር የተጠቃ መሆኑን ጠቅሰው፤ ወደ 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነው በጠንካራ አሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነና በኖራ መታከም ያለበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ጠንካራ አሲዳማ አፈር ስንል የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከ 5 ነጥብ 5 በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al3+) ካታየኖች የሚበዙበት አፈር ሲሆን፤ የእነዚህ ካታየኖች መብዛት የሰብሎችን ሥር በመመረዝ በዕድገታቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን እንደሚፈጥር ነው ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ የሚጠቁመው፡፡ ፒ ኤች መጠኑ ከሰባት ወደ ዜሮ እየቀነሰ ሲሄድ የአሲድነቱ ጥንካሬ የሚጨምር ሲሆን ከሰባት ወደ 14 ሲጨምር የጨዋማነቱ ባህሪ እንደሚጨምር ነው የዘርፉ ባለሙያዎች የሚያስቀምጡት። በአገራችን ሁኔታ አሲዳማ አፈርን ለማከም ኖራ መጠቀም የሚያስፈልገው የአፈሩ ፒ ኤች መጠን ከ5 ነጥብ 5 በታች ሲሆን ነዉ፡፡ ኖራ በተፈጥሮ የሚገኝ የካልሲየም እና የማግኒዚየም ካርቦኔት ሃይድሮኦክሳይድ ውህድ ሲሆን፤ አሲዳማ አፈር ውስጥ በሚጨመርበት ወቅት አሲዳማ አፈር ውስጥ የሚገኙትን አልሙኒየም እና ሃይድሮጂን አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በመግታት የአፈሩን ፒ ኤች መጠን ከፍ በማድረግ ለእፅዋት እድገት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ በአማካይ በአፈር አሲዳማነት የተጎዳ መሬትን ለማከም በሄክታር 30 ኩንታል የግብርና ኖራ እንደሚያስፈልግ ባለሙያዎች ይመክራሉ። በአሲዳማነት የተጠቃ መሬት አሲዳማነትን የሚቋቋሙ ሰብሎች ካልተዘሩበት ወይም አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ ካልተሰራ የሚሰጠውን የአፈር ማዳበሪያ ከጥቅም ውጭ በማድረግ ለኪሳራ ይዳርገናል ነው ያሉት፡፡ እንደ አኩሪ አተር፣ ካሳቫ፣ አናናስ፣ ዳጉሳ፣ ቡና፣ ሻይ እንዲሁም የስንዴ ዝርያዎች አሲድን የመቋቋም ባህሪ እንዳላቸውም ተመላክቷል፡፡ ግብርና ሚኒስቴር በአሲዳማነት ከተጠቃው 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነውን በአሥር ዓመት ውስጥ ለማከም ዕቅድ የያዘ ቢሆንም በዕቅዱ መሰረት በዓመት 400 ሺህ ሄክታር መሬት ለማከም ወደ 5 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት፡፡ ከበጀት አንጻር ይህን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በየዓመቱ ከመንግሥት ካዝና ማግኘት ከባድ በመሆኑ ከእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች፣ ከአጋር አካላት ድጋፍ ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ነው ያስታወቁት። ምንም እንኳን በአሲዳማነት የተጠቃውን አፈር ማከም ወጪው ከፍተኛ ቢሆንም አፈሩ ሳይታከም በቆየ ቁጥር ከምርት ውጭ የመሆን ዕድሉ እየጨመረ ስለሚሄድ አገርን የሚያሳጣው ዋጋ ከፍተኛ እንደሚሆን በውል መረዳት ያሻል። በዚህም የአፈር አሲዳማነት ጉዳይ መፍትሔ ካልተሰጠው ምርታማነትን ከ50 በመቶ እስከ 100 በመቶ ሊያሳጣ እንደሚችል ነው በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊው ፋኖሴ መኮንን የሚናገሩት፡፡ ከአፈር አሲዳማነት የተነሳ በየዓመቱ ወደ 9 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በኢትዮጵያ ደረጃ በስንዴ ከሚሸፈነው መሬት ብቻ እየታጣ እንደሆነ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ይህ በስንዴ ብቻ ከሚሸፈን መሬት የተወሰደ ግምት ሲሆን በገብስ፣ ጤፍ ወዘተ… ቢታሰብ ምን ያህል የምርት ማሽቆልቆል እንደሚያስከትል ማወቅ ይቻላል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ የስንዴ ምርት በአማካይ በሄክታር እስከ 40 ኩንታል ምርት ሊሰጥ ይችላል፤ ሆኖም ግን የአፈር ጤንነቱን በመጠበቅ አስፈላጊውን ግብአት የምንጠቀም ከሆነ በሄክታር 60 ኩንታል በማምረት አገራችን የጀመረችውን ምርትና ምርታማነትን የማረጋገጥ ሥራ ማከናወን ያስችለናል ነው ያሉት፡፡ ይህንንም ከግብ ለማድረስ የግብርና ሚኒስቴር የመጀመሪያው የትኩረት አቅጣጫው የአሲዳማ አፈር ልማት መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ ያስረዱት፡፡ አሲዳማ አፈሩን ለመከላከል በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ባለፉት ሦስት ዓመታት 38ሺህ 369 ሄክታር መሬት በኖራ የማከም ሥራ መከናወኑ ተገልጿል። ይህ ከሚኒስቴሩ ዕቅድ አኳያ ሲታይ በጣም ዝቅተኛ አፈጻጸም ነው። የአፈር አሲዳማነትን ለማከም የግብርና ኖራ ምርት ላይ የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች አቅርቦቱን በሚፈለገው ደረጃ ቢያቀርቡም፤ የኖራ ምርቱ በብዛት ያለበት ቦታ እና አሲዳማ መሬቱ የሚገኝበት ርቀት በተቃራኒው በመሆኑ ከትራንስፖርት አንጻር ያለው ችግር ሥራውን አድካሚ እንዳደረገው ነው የሚኒስቴሩ መረጃ የሚያመለክተው። ነገር ግን አርሶ አደሩ አንድ ጊዜ መሬቱን በኖራ ማከም ከቻለ እስከ አምስት ዓመት ሊያገለግለው ይችላል። ከዚያም በኃላ ቢሆን የተወሰነ የምርት መቀነስ እንጂ በምርታማነት ላይ የጎላ ችግር አይኖረውም ነው ያሉት። ስለሆነም ኖራን የመጠቀም ሁኔታ አቅም ያለው አርሶ አደር በግዥ መልክ እንዲጠቀም፤ አቅም የሌለው ደግሞ መንግሥት ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል። እንደ ምዕራብ ኦሮሚያ ነጁ፣ መንዲ፣ ምዕራብ ወለጋ እንዲሁም በአማራ ክልል አዊ ዞን፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አብዛኛውን ወረዳዎች በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጠቁ በመሆናቸው ምርት ለመስጠት የማይችሉበት ደረጃ ላይ እየደረሱ መሆኑን አቶ ፋኖሴ ገልጸዋል። ዝዋይ፣ ሐዋሳ፣ መራቤቴ፣ ደጀን፣ ጉደርና የመሳሰሉት በመንግሥትም ሆነ በግል የግብርና ኖራ ምርት የሚቀርብባቸው ቦታዎች መሆናቸው ነው የተጠቆመው። በእነዚህ ቦታዎች የምርትና የጥሬ ዕቃ ችግር የሌለና የግብርና ኖራ ዋጋም በኩንታል እስከ 350 ብር እየተሸጠ ነው ብለዋል። የአፈር አሲዳማነት በረዥም ጊዜ የተፈጥሮ መዛባት ሂደት ውስጥ የሚከሰት እንደመሆኑ መጠን አንዴ ችግሩ ከተከሰተ በኋላ መፍትሔ በመስጠት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ወጪ እና ርብርብ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም ችግሩ ከመከሰቱ በፊት የአፈር አሲዳማነትን ለመከላከል የሚያስችሉ እርምጃዎችን መውሰድ ተገቢነት ያለው ጉዳይ እንደሆነ ነው የተጠቆመው፡፡ መንግሥት በያዘው የሌማት ትሩፋትና የግብርና ኢኮኖሚ አቅጣጫ በተለይም የስንዴ ምርት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለሌሎች አገራት ምርቱን በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት በሚደረገው ጥረት የአፈር ምርታማነትን/ጤንነቱን መጠበቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑ የግድ ነው። “ለም አፈር በሌለበት ምርትና ምርታማነት የማይታሰብ ነው” የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ ግብርና የመሪነት ተግባሩን እንዲወጣ በቅድሚያ የአፈር ጤንነት ሊጠበቅ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም ከዚህ በፊት ያለውን የግንዛቤ ችግርና ከአመራሩ እስከ አርሶ አደሩ ያለውን ክፍተት በመቅረፍ ችግሩን ለመቀነስ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል። ሁሉንም ነገር ከመንግሥት መጠበቅ የለብንም የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ በቅድመ-መከላከል ሥራ ችግኝ በመትከል፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ በማከናወን፣ በተፈጥሮ ማዳበሪያ (ኮምፖስት) የራስን ማሳ በመንከባከብ፣ አማራጭ ሰብሎችን እያፈራረቁ በመዝራት፣ አሲዳማነትን መቋቋም የሚችሉ ተክሎችን በመምረጥ ማልማት እንዲሁም የግብርና ኖራ በመጠቀም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል። በሀገራችን በተለያዩ የምርምር ተቋማት የተሰሩ ምርምሮች እንደሚያሳዩት አሲዳማ አፈርን ለማከም የተፈጥሮ ማዳበሪያዎችን ከኖራ ጋር አቀናጅቶ በመጠቀም በዋና ዋና ሰብሎች ላይ እስከ ሁለት እጥፍ የምርት ጭማሪ ማግኘት እንደሚቻል ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በመሆኑም አርሶ አደሮች ኖራ በግዥና በብድር የሚያገኙበትን ሥርዓት በተጠናከረ አግባብ መተግበር ያስፈልጋል። ልክ እንደ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በግዥ ወይም በብድር የግብርና ኖራ በማቅረብና በአሲዳማነት የተጎዳው መሬት እንዲያገግም ማድረግ ላይ አትኩሮ መስራት ሌላው የመፍትሄ አካል ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል። የእርሻ መሬት አያያዝና እንክብካቤ ጉዳይ የህግ ማዕቀፍ ኖሮት በዚያ አግባብ ተግባራዊ ማድረግም በተለይ በአሲዳማነት የመጠቃት አዝማሚያ የተጋረጠበትን የእርሻ መሬት ለመታደግና የተጎዳውንም እንዲያገግም ለማከም የሚሰሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ያስፈልገዋል። ከዚህ ባለፈም በአንድ የእርሻ ቦታ ላይ የተለያዩ ሰብሎችን መዝራት፣ አፈር ውስጥ ህይወት ያላቸው ነገሮች እንዲኖሩ ማድረግና የአፈሩን እርጥበታማነት ማዝለቅ ተገቢ ይሆናል።
አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታና አብሮነት
May 3, 2023 1059
በጣፋጩ ሰለሞን አገራችን ኢትዮጵያ የተለያየ ቋንቋ፣ ባህልና እምነት ያላቸው በርካታ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ተቻችለው፣ ተከባብረው፣ ተዋደው፣ በአንድነትና በአብሮነት በፍቅር የሚኖርባት አገር ነች። በዚህም የብሄር ብሄረሰቦች ሙዝዬም ነች የሚል አድናቆትን ተጎናፅፋለች-ኢትዮጵያ። እነዚህ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች የራሰቸው መገለጫ የሆኑ ቱባ ባህል አላቸው። ኢትዮጵያውያን ለዘመኑ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጥበብ መሰረት የሆኑ የአያሌ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤቶች ናቸው። ባህላዊ የመድኃኒት ቅመማና የህክምና ጥበብ ኢትዮጵያ ለዓለም ካበረከተቻቸው ትሩፋቶች መካከል አገር በቀል ዕውቀቶች ተጠቃሽ እንደሆኑ የታሪክ ድርሳናትና ሌሎች የየዘርፉ ተጓዳኝ መረጃዎች ያስረዳሉ። በተለይ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የተጠቀሙባቸውና እየተጠቀሙባቸው ያሉ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሌሎችም ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀሱ ናቸው። በጂንካ ዩኒቨርስቲ 5ኛው አገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ ሰሞኑን ተካሂዷል። በኮንፈረንሱ በአገር በቀል ግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም፣ለአብሮነት ትስስር እና ለአገራዊ ዕድገት ያላቸው ሚና የሚል እሳቤን ዓላማ ያደረገ ጥናት ቀርቧል። ጥናቱ እ.ኤ.አ ከ2018 እስከ 2022 ባሉ ዓመታት በመስቃን እና በማረቆ ህዝቦች ባህላዊ የግጭት አፈታት ላይ መሰረት አድርጎ የተካሄደ ነው። ጥናቱን ያካሄዱት "አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሰላም፣ ለፀጥታ እና ለዕድገት ያላቸው አስተዋፅኦ፤The Role of Indigenous conflict resolution Mechanism for peace,Security ,and Sustainable Development in Ethiopia " በሚል ርዕስ ያካሄዱት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ ዮሐንስ ተስፋዬ ናቸው። የጥናቱ ግኝት እንደሚያመለክተው ዘመናትን ተሻግረው እዚህ የደረሱ የሰላም ግንባታና ማጠናከሪያ የሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች አሁን ለደረስንበት ሳይንሳዊ ጥበብ መጎልበት እያገለገሉ ነው። የጥናት አቅራቢው ለኮንፈረንሱ ታዳሚዎች እንዳብራሩት ጥናቱ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ለአብሮነትና ለዕድገት አይተኬ ሚና አላቸው። እነዚህን አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች በአግባቡ መጠቀም ይገባል። እሳቸው እንዳብራሩት በአገራችን ሶስት አይነት የግጭት አፈታት ዘዴዎችን እንጠቀማለን። የወንጀልና የፍትሐብሔር ህጎች፣ እንደ ሽምግልና ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች እና ከሃይማኖታዊው ደግሞ ሸርዓ ከምንጠቀምባቸው የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ናቸው። ተመራማሪ ዮሐንስ እንዳሉት ጥናቱ በተካሄደበት በጉራጌ ዞን በመስቃን እና በማረቆ መካከል አጋጥሞ የነበረውን አለመግባባት ከመፍታት አኳያ ከዘመናዊ እውቀቶች ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ትልቅ ሚና ነበራቸው። በመስቃን እና በማረቆ ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት ከመስቃን፤ ከማረቆ እንዲሁም ከአጎራባች የኦሮሚያና ስልጤ ዞኖች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል። በመስቃን እና በማረቆ መካከል ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት የተሳተፉት የሀይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች ግጭቱን ለመፍታት የተጠቀሙት ጥበብ አገር በቀል ዕውቀቶች በዘመናዊ ህግና አሰራር የማይቻሉትን የመፈጸምና ማህበራዊ አንድነትን ከማጠናከር አንፃር ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የጥናቱ ግኝት አመላክቷል። አለመግባባቱን ለመፍታት 26 ዙር ለመሸምገል ተቀምጠዋል። በማሸማገሉ ሂደት የተሳተፉት የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሁለቱን ማህበረሰቦች ለማቀራረብና በአካባቢው እረቀ-ሰላም ለማወርድ የከፈሉት መስዋዕትነት ቀላል አለመሆኑን በአጽኖኦት አስረድተዋል። የትኛውንም ውጣ ውረድና ጫና ተቋቁመው ሳይታክቱ ችግሩን የፈቱበት መንገድ ለዘመናዊው አስተዳደር ትምህርት የሚሰጥና በቅርስነት ለትውልድ የሚተላለፍ ሰናይ ተግባር መሆኑንም አስረድተዋል። ግጭቶች ቀደም ሲል የነበሩ፣ አሁንም ያሉና ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው። በተለያዩ ምክንያቶች የሚያጋጥሙ ግጭቶችን ፖለቲካዊ ትርጉም በመስጠት ከማጦዝ ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ተጠቅሞ ለማርገብ መስራት አዋጭና ተመራጭ መንገድ መሆኑን የጥናቱን ግኝት ዋቢ አድርገው ተመራማሪ ዮሐንስ መክረዋል። ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ለአገር በቀል እውቀቶች ተገቢውን ዕውቅና መስጠት ይገባል። አገር በቀል ዕውቀቶችን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ አካቶ ለማጎልበት የተጀመረው አበረታች ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል። አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ አብሮነትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው ያሉት ደግሞ የጂንካ ዩኒቨርስቲ የባህል ተመራማሪና የዩኒቨርስቲው የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ኤሊያስ ዓለሙ ናቸው። አክለውም ዘመናዊ ሕግን ተከትሎ በሚሰጡ ብያኔዎች አንዱ ወገን የሚደሰትበት ሌላኛው ደግሞ ቅር ተሰኝቶ የሚከፋበት ናቸው ይላሉ። በማህበራዊ ሸንጎ ግን ሁለቱም ወገን የሚደሰቱበት፣ ከልብ ይቅር ተባብለው ችግሮቻቸውን የሚፈቱበትና ዘላቂ እርቀ-ሰላም የሚያወርዱበት እንደሆነም ያስረዳሉ። ዶክተር ኤሊያስ አክለውም ይህም ማህበራዊ አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው የላቀ ነው። የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታትና በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በአገራችን ቱባ ባህሎች ውስጥ ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን መጠቀም ይገባል። በባህላዊ እሴቶቻችን ውስጥ ያሉ አገር በቀል ዕውቀቶች ቀጣይነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ እንዲውሉና ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆኑ ዕውቅና መስጠት፣ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ማካተት፣ በአግባቡ አደራጅቶና ሰንዶ ለትውልድ ማስቀመጥ እንደሚገባ አመላክተዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራን የሚጠበቅብንን ኃላፊነት በአግባቡ ልንወጣ ይገባል ይላሉ። አቶ መምህሩ ገዙሜ በጂንካ ዩኒቨርስቲ በሶሻል አንትሮፖሎጂ የትምህርት ክፍል የሶሽዮሎጂ መምህር ናቸው። አገር በቀል ዕውቀቶች ለአገራዊ ችግሮቻችን መፍቻ መንገዶች ናቸው ይላሉ። የሳይንሳዊ ምርምሮች ፅንሰ-ሀሳብ መነሻው አገር በቀል ዕውቀቶች እንደሆኑ ይጠቅሳሉ። በአገራችን በርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ቢኖሩም እንዳለመታደል በአግባቡ መጠቀም አልቻልንም ሲሉም ያክላሉ። እሳቸው እንዳሉት መንግሥት አሁን ለአገር በቀል ዕውቀቶች የሰጠው ዕውቅና ለአገር በቀል ዕውቀቶች መጎልበትና ጥቅም ላይ መዋል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይህን ዕድል በመጠቀም አገር በቀል እውቀቶች ጎልተው እንዲወጡና በትምህርት ሥርዓቱ ተካተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት ይገባል። በተለይ የማህበረሰቡ የግጭት አፈታት ዘዴና በምክክር ችግሮችን የመፍታት ጥበብ የታሰበው አገራዊ የምክክር መድረክ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። በመሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ፣ ለኢትዮጵያውያን የአብሮነት ትስስርና መስተጋብር መጠንከር እንዲሁም ለአገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና እጅግ የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ተገንዝቦ ተገቢውን ዕውቅና በመስጠት መጠቀም ይገባል።
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ
Apr 2, 2023 1781
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ በሰለሞን ተሰራ በታሪክ ተመዝግበው የምናገኛቸው አያሌ መልካምና በጎ ነገሮች የመኖራቸውን ያህል በተቃራኒው ደግሞ የሰው ልጆች ግፍና በደል ሲፈጽሙና ሲያስተናግዱ ኖረዋል። በዚህም በተለይ በበደሉ ገፈት ቀማሾች ላይ የሚደርሰው ድንጋጤ፣ ሰቆቃና ሀዘን ሰዎችን ለበቀል እያነሳሳ ሌላ ጥፋት ሲያስከትል ማስተዋልም እንግዳ ነገር አይደለም። በዚያው ልክ ሰዎች የደረሰባቸውን ግፍና መከራ ለማራገፍ ፍትህን ሲሹና ሲጠይቁ ይስተዋላል። እምባቸው የሚታበሰው፣ ቁስላቸው የሚሽረው ለደረሰባቸው በደል ካሳ የሚሆን ፍትህ ሲያገኙ ብቻ እንደሆነም ያምናሉ። በርካታ አገራትም በታሪክ ውስጥ ላጋጠሟቸው ስብራቶች የሽግግር ፍትህን አማራጭ አድርገው በመጠቀም ለችግሮቻቸው መፍትሄ ያበጃሉ። እኤአ በ1970 ዎቹ መጀመሪያ በምስራቅ አውሮፓ እና ደቡብ አሜሪካ ተግባራዊ በተደረገው የሽግግር ፍትህ በጦርነትና በግፍ አገዛዝ የተበደሉ አካላት ፍትህ እንዲያገኙ የተደረገበት መንገድ ተጠቃሽ ነው። ከዚህ ጊዜ በኋላ የሽግግር ፍትህ በተለይ በመደበኛ የህግ ስርአት ብቻ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስቸግሩ ጉዳዮችን ጭምር በተጠያቂነት፣ በይቅርታ፣ በካሳ ወዘተ መፍትሄ በመስጠት የፍትህ ማስፈኛ መንገድ ተደርጎ ተወስዷል። የሽግግር ፍትህ ማለት በማህበረሰቡ ውስጥ በስፋት ለተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ምላሽ የሚሰጥበት አካሄድ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ። ይህንን ሂደት ሰላማዊ፣ አካታችና ተደራሽ ለማድረግ የሁሉም ጥረትና አጋርነት ቀዳሚ መነሻ ሊሆን እንደሚገባውም ይገልጻሉ። የሽግግር ፍትህ በአንድ ጊዜ የሚያልቅ ሳይሆን ጊዜ የሚጠይቅና ዓመታትን ሊወስድ የሚችል ነው። ይህም ለተበዳዮች ፍትህ በመስጠት፣ ካሳ በመክፈል፣ የወደሙ ንብረቶችን መልሶ በመገንባትና በመሰል ሂደቶች ሊፈጸም ይችላል። የሽግግር ፍትህ ሀገራት ከብጥብጥ፣ ከፀብና ጥላቻ አዙሪት እንዲወጡ በማድረግ በኩል የማይተካ ሚና እንዳለው የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮዎች ያሳዩናል። በ2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ የፀደቀው የአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማዕቀፍ፣ የሽግግር ፍትህ ሀገራት የተለያዩ መደበኛ እና ባህላዊ ወይም መደበኛ ያልሆኑ የፖሊሲ እርምጃዎችንና ተቋማዊ አሠራሮችን በመጠቀም የተፈጸሙ ጥሰቶችን፣ ክፍፍሎችንና አለመመጣጠኖችን ለማስወገድና ለደኅንነትም ሆነ ለዴሞክራሲያዊና ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሥርዓት ግንባታ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የሚደረግ ጠቃሚ እና አስፈላጊ ሂደት እንደሆነ ይገልጻል። የሽግግር ፍትህ በግጭት፣ በጦርነት ወይም ጨቋኝ ሥርዓት በነበረበት ወቅት ለተፈፀመ ጥቃት፣ መጠነ-ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና በደል የተሟላ መፍትሄ መስጠት መቻል ነው። ይህም በዋናነት ሙሉ ፍትህ የሚሰጥበትን መንገድ በመዘርጋት ዘላቂ ሰላም፣ እርቅ፣ መረጋጋት እና የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት መገንባት የሚቻልበትን ሁኔታ የሚመለከት ነው። በኢትዮጵያ ተግባራዊ ሊደረግ የታሰበውና በፖሊሲ አማራጭ ዝግጅት ሂደት ላይ የሚገኘው የሽግግር ፍትሕ በአራት ዋና ዋና ምክንያቶች አስፈላጊ መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። አንደኛው ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሀገራዊ አውድ ሲሆን በዚህም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ አለመረጋጋት፣ ግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት ተከስቷል። ይህም ዜጎችን ለሞት፣ ለአካል ጉዳት፣ ለመፈናቀል ያጋለጠ መሆኑ በገፊ ምክንያትነት ይጠቀሳል። ለነዚህ ችግሮች ከዚህ በፊት የተሰጡ ምላሾች ሙሉ አለመሆናቸው የአጥፊዎችና የተጎጂዎችን ቁጥር ማብዛቱ፣ የበደሎች መደራረብ እና የጥፋቶች ማህበረሰባዊ ቅርጽ መያዝ በመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት እና አካሄድ ፍትሕ መስጠትንም ሆነ ይቅርታ እና እርቅን ማከናወን አላስችል ማለቱ የሽግግር ፍትህ ትኩረት እንዲሰጠው አድርጓል። ሁለተኛው የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ማለትም ባለፉ በደሎች ይቅር ለመባባል፣ እርቅ ለማውረድ፣ ሕዝብ ለማቀራረብ፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እና ለተፈጸመ በደል እውቅና ለመስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ነው። ሶስተኛው ምክንያት የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ሳይተገበር የዴሞክራሲ ሽግግርም ሆነ ዘላቂ ሰላም ማስፈን አይቻልም የሚል ነው። የመጨረሻው በገፊ ምክንያትነት የሚጠቀሰው ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሽግግር ፍትህ ወሳኝ በመሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በነዚህ ምክንያቶች የሽግግር ፍትሕን ለማስፈን እየሰራች መሆኑ በበርካቶች ዘንድ በአዎንታዊ መልክ ይጠቀሳል። በተለይ የሽግግር ፍትህን ተግባራዊ ካደረጉ አገራት ተሞክሮ በመውሰድ ለውጤታማነቱ ከተሰራ በርግጥም አይነተኛ መፍትሄ ነው። ከአፍሪካ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ደግሞ ጋምቢያ የሽግግር ፍትህን ለችግሮቻቸው መፍቻነት ከተጠቀሙ አገራት መካከል ናቸው። ሩዋንዳ ሩዋንዳ እኤአ በ1994 በመቶ ቀናት ብቻ ከነበሯት 7 ሚሊዮን ዜጎቿ 800 ሺዎቹን በግፍ ተነጥቃለች። 2 ሚሊዮን የሚጠጉት በስደት ሀገራቸውን ለቀው ሲወጡ በዚህ የጭካኔ ተግባር ተሳትፎ ነበራቸው የተባሉ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ላይ ክስ በመመስረት ፍትህ ፊት አቅርባቸዋለች። በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት በሀገር ውስጥ ችሎትና በባህላዊ መንገድ በተዳኙት ወንጀለኞች ላይ የተሰጡት የፍትህ ውሳኔዎች አሁን ላይ ሀገሪቱን በዲሞክራሲና በሰላም እንዲሁም በብልፅግና መንገድ መራመድ እንድትችል አድርጓታል። ሩዋንዳውያን በቆየ ሀገራዊ ብሂላቸው ”ሁላችንም የአንድ አባትና እናት ልጆች ነን ይላሉ”። ይህንኑ ብሂል መመሪያቸው በማድረግ በሀገሪቱ ያሉት “ቱትሲ” እና “ሁቱ” የተባሉት ዋነኛ ብሄሮች በአብሮነት ለዘመናት ኖረዋል። ሩዋንዳ በጀርመን የቅኝ አገዛዝ ስር እንደወደቀች የዘር ልዩነቱን ወደፊት ያመጡት ቅኝ ገዥዎች ሁለቱን ብሄሮች የሚያጋጩ ሴራዎችን በመጎንጎን ቱትሲዎችን መግደል የፖለቲካቸው ስልት ማስፈጸሚያ አደረጉት። ይህ ከፋፋይ የፖለቲካ ሴራ በቤልጂየም የእጅ አዙር አገዛዝ ዘመንም እንደቀጠለ ይነገራል። በዚህም ማንነትን መሰረት ያደረገ የፖለቲካ አደረጃጃት፣ የመታወቂያ ወረቀት፣ ቱቲስዎችን በስልጣን ወደፊት ማምጣትና ሁቱዎችን አሳንሶ መመልከትን ባህል አደረጉት። በዚሁ መርዘኛ ሀሳብ መነሻነት ከነጻነት በኋላ እኤአ ከ1959 እስከ 1967 አካባቢ በመንግስት በተደገፈ የዘር ማጥፋት 20ሺ የሚጠጉ ቱትሲዎች ሲገደሉ 300ሺ የሚጠጉ ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዱ። በዚህም እኤአ በ1987 በቱትሲዎችና ለዘብተኛ ሁቱዎች የተቋቋመው የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር እኤአ በ1993 የመንግስትን ስልጣን ለመጋራት በቃ። ነገር ግን እኤአ በሚያዚያ 6 ቀን 1994 የሀገሪቱ መሪ የነበሩት ሃባይሪማና በቅጥረኞች በመገደላቸው በሀገሪቱ አመጽ እንዲቀጣጠል ምክንያት ሆነ። ይህን ተከትሎ “ኢንተርሀሞይ” በመባል የሚጠራው የሚሊሽያ ቡድን በቱትሲዎችና በለዘብተኛ ሁቱዎች ላይ ዘመን የማይሽረው ግፍና ጭካኔ በመፈጸም 800ሺ የሚጠጉትን ከምድር ላይ ለዘለአለሙ አሰናብቷቸዋል። ይህ ደግሞ የዘር ማጥፋት ወንጀል በመሆኑ አጥፊዎቹ በተለያዩ የፍትህ አደባባዮች ተከሰው ቅጣታቸውን ለመቀበል በቅተዋል። ነገር ግን ይህ ብቻውን በህዝቡ ውስጥ ስር የሰደደውን ቁስል እንዳማይሽረው በመታመኑ ሩዋንዳ የሽግግር ፍትህን በመከተል አመርቂ ስራ ሰርታለች። በተለይም ክስና ይቅርታ ትልቅ ቦታ ነበራቸው። በክስ ሂደቱ ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ ቢከብድም በዋናነት ተሳታፊ የነበሩትን በመለየትና ተጠያቂ በማድረግ ፍትህ እንዲሰፍን ተደርጓል። መንግስት ውጫዊና ውስጣዊ ግፊት ቢበዛበትም ከፍተኛ ግፍ የፈጸሙትን በመለየት እንዲቀጡ አድርጓል። ይቅርታውንም በተጠና መንገድ በማከናወን ለጥቂቶች ምህረት አድርጓል። በጊዜ ሂደት የእስራት ጊዜአቸውን ላገባደዱ፣ ለአዛውንቶች፣ ለታማሚዎችና ለወጣቶች ምህረት በማድረግ ቁርሾው እንዲሽር ተደርጓል። ምህረት የተደረገላቸው ሰዎች ስለብሄራዊ እርቅ፣ አብሮነት፣ ሀገራዊ ማንነትና ሰብዓዊ ክብር እንዲማሩ በማድረግ እርቁን ሙሉ ማድረግ ተችሏል። የሩዋንዳ የሽግግር ፍትህ በዋናነት እውነትን ማፈላለግ፣ ነገሮችን መልሶ ማስታወስ ወይም የመታሰቢያ ቦታዎችን በመመስረትና ቀን በመሰየም ሁኔታው ታስቦ እንዲውል ማድረግ፣ መልሶ ማቋቋምና እርቅ ማውረድ የተቋማት ማሻሻያ ማድረግ ላይ ያተኮረ ነበር። ሴራሊዮን እኤአ ከ1991 አስከ 2002 የዘለቀው የሴራሊዮን የእርስ በርስ ግጭት በትንሹ የ100ሺ ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ አልፏል። ሌሎች በ100ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችን ለከፋ የአካል ጉዳት፣ ድህነትና የአዕምሮ መቃወስ ዳርጓል። ግጭቱ የተጀመረው ራሱን “የተባበሩት አብዮታዊ ቡድን” ብሎ በሚጠራው የታጣቂዎች ስብስብ ሲሆን በወቅቱ ቡድኑ በላይቤሪያ መንግስት ይደገፍ እንደነበር ይነገራል። የተቃውሞአቸው መነሻ ደግሞ የመንግስት ብልሹ አስተዳደር፣ የገጠሩ ማህበረሰብ ከኢኮኖሚና ፖለቲካ ተሳትፎ መገለል እና መጠነ ሰፊ የህግ ጥሰቶች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ። የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሃብት በተለይም የአልማዝ ማዕድኗን በህገወጥ መልኩ ሲበዘብዙ የነበሩ አመራሮች ቁርሾውን በማባባስ ህልውናቸውን ለማስቀጠል ቢጥሩም እኤአ በ2002 በተደረሰ የሰላም ስምምነት ከ 76 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን በማስረከብ ህብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ ተደርገዋል። በዚያው ዓመት የሴራሊዮን የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን የተቋቋመ ሲሆን በተመሳሳይ የሴራሊዮን ልዩ ችሎት ተመስርቷል። ሴራሊዮን በእርስ በርስ ግጭት ውስጥ በነበረችባቸው 12 ዓመታት አራት መፈንቅለ መንግስት የተካሄደባት ሲሆን የስልጣን መንበሩን የተፈራረቁበት የተለያዩ ወታደራዊ አመራሮች ለችግሩ መፍትሄ ከማበጀት ይልቅ በቤንዚን ላይ እሳት የሚያርከፈክፉ ሆነው ታይተዋል። በሴራሊዮን ለደረሰው እልቂት እኩል ኃላፊነት የሚወስዱት መንግስትና ታጣቂዎች በወቅቱ ሴቶችን በመድፈር፣ ህፃናትን በግዳጅ ለጦርነት በመመልመል፣ ንብረት በማውደምና በ100ሺ ለሚቆጠሩ ሰዎች መሞት ተጠያቂ ተደርገዋል። ከዚህ ባለፈ በቅድሚያ ታጣቂዎችን የጦር መሳሪያ ለማስፈታት የተሄደበት ርቀት ለሰላም መስፈን ትልቅ እገዛ ማድረጉ የሚገለጽ ሲሆን ከ70 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎችን መሳሪያ ማስፈታት መቻሉ ግጭቱን ለማስቆም በራሱ ታላቅ ስኬት ነበረው። በወቅቱ ግፉን የፈጸሙት ታጣቂዎች በመንግስት ቅጣታቸውን እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን ህብረተሰቡም ወንጀለኞችን ከማህበረሰቡ በማግለል የስነ ልቦና ቅጣት እንደጣለባቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በዚህም ታጣቂዎቹን ወደ ህብረተሰቡ መልሶ ለመቀላቀል የተደረገው ጥረት በፈተና ቢታጀብም በህዝቡ ይሁንታ ውጤታማ ሆኗል። በሴራሊዮን የሽግግር ፍትህን ለማስፈን የተቋቋሙት የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን፣ የሴራሊዮን ልዩ ፍርድ ቤት፣ በፀጥታ ተቋማት ላይ የተደረገው ማሻሻያ፣ የመልሶ ማቋቋምና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምስረታ ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው። የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን በተሰጠው ስልጣን መሰረት ተጎጂዎችን ከሰቆቃ መታደግና ችግሩን በዕርቅ መፍታት፣ ብዙሀኑ ላይ ለደረሰው ግፍ ምላሽ መስጠት፣ ግፉ በቀጣይ እንዳይደገም መፍትሄ ማበጀት ላይ አተኩሮ ሰርቷል፡፡ በዚህም ከተጎጂዎች ቃለ ምልልስ በመነሳት በደረሰበት ድምዳሜ የመንግስት አካላት የመልካም አስተዳደር መጓደል፣ ሙስና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ከነፃነት በኋላ የነበረው አመራር ብቃት ማነስ ለብጥብጡ መንስኤ እንደሆነ አመላክቷል። ልዩ ፍርድ ቤቱም በቅድሚያ ተጎጂዎችን ሰብስቦ በማናገር እንዲሁም የሲቪል ማህበራትን ህብረተሰቡንና መገናኛ ብዙሃንን በማካተት ሁሉንም የሚያስማማ ውሳኔ በመስጠት ችግሩ ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ መፍትሄ እንዲያገኝ አስችሏል። የመልሶ ማቋቋም ሂደቱ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበርና ልዩ በጀት በመመደብ የተከናወነ ሲሆን የተጎጂዎችን ሰቆቃ ሊጠግን በሚችል መልኩ መተግበሩንም ብዙዎች ይመሰክራሉ። በዚህም ተጎጂዎች ነፃ የጤና አገልገሎት፣ ትምህርት፣ መኖሪያ ቤትና መቋቋሚያ እንዲያገኙ ተደርጓል። በአብነት የተነሱት የሩዋንዳና ሴራሊዮን ተሞክሮዎች የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭቶችን ያስተናገዱ ሀገራት የተሻለ ነገን እንዲገነቡ ሁነኛ መፍትሔ ስለመሆኑ አመላካች ናቸው። በተመሳሳይ የሽግግር ሂደት ያለፉና ተሞክሮ ያላቸው የደቡብ አፍሪካ እና ጋምቢያ ምሁራንም ይህንኑ እውነት የሚያረጋግጥ ሀሳባቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። በደቡብ አፍሪካው ፍሪታውን ዩኒቨርሲቲ የፍትሕና ዕርቅ ኢንስቲትዩት ኃላፊ እና በአፍሪካ ጥናትና ምርምር የካበተ ልምድ ያላቸው ፕሮፌሰር ቲም ሙሪቲ በአፍሪካ ሽግግር ፍትህ ዙሪያ ጥልቅ ምርምር አድርገዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊና የአፍሪካ ተምሳሌት ሀገር ናት የሚሉት ፕሮፌሰሩ፤ የገጠማትን ችግር ለመፍታት የሽግግር ፍትህ ሂደት መጀመሯን አድንቀዋል። የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭትና ግፎችን ባሳለፉ ማህበረሰቦች ትናንትን በይቅርታ የነገውን ተሰፋ ለመሻገር አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን በማንሳት ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ፣ ባርነት እና ቅኝ ግዛት የጭቆና ስርዓት ነጻ ስትወጣ ስርዓቱ በጥቁሮች ላይ ለፈጸመው ግፍ፣ መገለልና ብዝበዛ መፍትሄ ለመስጠት ሽግግር ፍትህ ሂደት መተግበሩን ይጠቅሳሉ። ፕሮፌሰር ሙሪቲ፤ የወቅቱ ፕሬዝዳንት ኔልሰን ማንዴላ በጥቁሮች ላይ የተፈጸሙ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት መልክ ለመስጠት ብሎም ህዝባዊ አብሮነት እንዲቀጥል በሊቀጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ መሪነት የዕውነትና ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን መቋቋሙን ያስታውሳሉ። የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ ከአፈጻጸም ጋር የተያያዙ ክፍተቶች ቢኖሩበትም አካታችና የአገሪቱን የቀጣይ ጉዞ ለመቀየስ መሰረት የጣለ እንደነበር ገልጸዋል። ይህም ኢትዮጵያ ተሞክሮ ልታደርገው የምትችለው ነው ይላሉ። በጋምቢያ በቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜህ ዘመነ መንግስት ለ22 ዓመታት የተፈጸሙ ግፎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት የፈቱት የዕውነት፣ ዕርቅና ካሳ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ጋምቢያዊው ዶክተር ባባ ጋሌህ ጃሎው፤ የሽግግር ፍትህ አስፈላጊነት በተለይም ኢትዮጵያን ለመሰሉ ሀገራት አጠያያቂ አለመሆኑን ይላሉ። በተመሳሳይ በጋምቢያ አምባገነን መንግስት የተፈጸሙ በደሎችን መልክ ለማስያዝ የተቋቋመው የዕውነት፣ ዕርቀ ሰላምና ካሳ ኮሚሽን ዜጎች ዕውነቱን እንዲረዱ፣ በዳዮች እንዲጠየቁና ተበዳዮች እንዲካሱ የሚያስችል ሰነድ ለሀገሪቷ መንግስት ማቅረቡን ዶክተር ባባ ጋሌህ ይገልጻሉ። እነዚህ ምሁራን ኢትዮጵያ ለማድረግ ያሰበችው የሽግግር ፍትህ ሂደት ከአፍሪካ ሕብረት የሽግግር ፍትሕ ፖለሲ እና የሀገራትን ልምድ የቀመረ፣ አካታች፣ ተበዳዮችን የሚክስና ሀገርና ህዝብ ወደፊት በሚያሻግር አግባብ እንዲፈጸም አስተያየታቸውን ጠቁመዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራኑ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለሚመለከተው አካል እንደሚያጋሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያን ባለፉት ጥቂት ዓመታት በህዝቦች የተባበረ ክንድ ለውጥ በማምጣት አዲስ ምእራፍ የጀመርንበት፣ አዲስ መንግስት ስልጣን ተቀብሎ ያለፉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በይፋ በማመን ይህንኑ ለማሻሻል ቃል የገባበት፣ የዲሞክራሲ ሽግግር ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት የተጀመሩበት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት የደረሱ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ለማለፍ መንገድ የጀመርንበት ወቅት ላይ መሆናችን ይታወቃል። የሽግግር ፍትህ የተበዳዮችን እምባ ከማበስ ባለፈ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ በማስቀመጥ ከቂም በቀል የጸዳ ትውልድ ለመፍጠርና ለአገረ መንግስት ግንባታ በጋራ ለመሰለፍ መፍትሄ መሆኑን ከላይ የተጠቀሱት አብነቶች ምስክሮች ናቸው። ለአፍሪካ ጉዳዮች አፍሪካዊ መፍትሄን የምታስቀድመው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ተሞክሮዎችን በመቀመር፣ ካለፈችባቸው መንገዶች ትምህርት በመውሰድ፣ ውጤታማ የሆነ የሽግግር ፍትህ ስርዓትን እውን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። የሽግግር ፍትሕ በተለይም በሽግግር ላይ ያሉ ሀገራት ህዝቦች ከነበሩበት ግጭት እንዲሁም ከደረሰባቸው ግፍ እና ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ወጥተው ወደ አዲስ ሰላማዊ እና አብሮነት ጉዞ ለመጀመር የሚደረግ የፍትሕ ክዋኔ አይነት በመሆኑ በትኩረት ሊሰራበት ይገባል።
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 3265
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
ትንታኔዎች
የረቂቅ ሙዚቀኛዋ መናኒት ሲታወሱ
Jun 2, 2023 188
የረቂቅ ሙዚቀኛዋ መናኒት ሲታወሱ አየለ ያረጋል መንደርደሪያ... እማሆይ ጽጌማርያም 'ዓለም በቃኝ' ብለው በምንኩስና ሕይወት መንነዋል። በቅድመ ምነናም ሆነ ድሕረ ምነና ሕይወታቸው ግን በረቂቅ ሙዚቃ ከመራቀቅ ቦዝነው አያውቁም ነበር። ለዚህ ነው 'የረቂቅ ሙዚቃ ተራቃቂዋ መናኒት' የሚሰኙት። በእማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ ፋውንዴሽን ድጋፍ ሰሞኑን በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 'ዝክረ እማሆይ ጽጌማርያም' መርሐ ግብር ተደርጎ ነበር። የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች መርሐ ግብሩን አሰናድተዋል። በሕይወት ዘመናቸው ከ300 በላይ የረቂቅ ሙዚቃ ስራዎችን ለአድማጭ ጆሮ ያበረከቱት እማሆይ ጽጌማርያም ያረፉት ባሳለፍነው መጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ነበር። ስርዓት ቀብራችው የተፈጸመውም ለ40 ዓመታት በገዳማዊ ሕይወት በኖሩባት ሀገረ-እስራኤል ኢየሩሳሌም ነው። የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ስያሜውን 'እማሆይ ጽጌማርያም የሙዚቃ ትምህርት ክፍል' በሚል ሰይሟል። እኛም እማሆይን በወፍ በረር መዘከር ወደድን!! የ'የውብዳር' ሙዚቃ ልክፍት ሙዚቃ ኅይል ነው-ውስጥን የሚፈነቅል፤ መንፈስን የሚሰረስር። የየውብዳር የሙዚቃ ውበትና ቃና ልክፍትም በዘመነ ደቂቅነት የተጸነሰ ነው። የሙዚቃ ፍቅራቸው ጠሊቅ፣ ስራቸውም ረቂቅ ነው። ግና በጨቅላነት የ'ግዳይ ጣይ' አዳኞችን ባህላዊ ዜማ ተከትለው ሮጠዋል። በቤተ ክርስቲያን ማህሌታዊ ዜማዎች ቀልብና ልባቸው ተማርኳል። የልጅነት ዕዝነ ልቦናቸው በሙዚቃ ቃና ተለክፏል። የደቂቅነት ዐይነ ልቦናቸው ተፈጥሯዊ ውበት በረቂቅ ሙዚቃ እንዲራቀቁ ሰበብ ሆኗቸዋል። 'ከሰፈር እስከ ማዶ-ሀገር' ኑረታቸው በዕዝነ ልቦናቸው ያቃጨለ የድምጽ ርግብግቢት በረቂቅ ሙዚቃ እንዲመንኑ መሰረት ሆኗቸዋል። የየውብዳር ዑደት ሕይወት ከዓለማዊ ወደ ሰማያዊ ሕይወት ብቻ ሳይሆን በመሳሪያ ወደ ተቀነባበሩ ረቂቅ ሙዚቃ ዳርቻም መንኗል። የወላጅ እናታቸው ካሳዬ የለምቱ በገና ደርዳሪነት፣ የአባታቸው ከንቲባ ገብሩ ደስታ የረቂቅ ሙዚቃ አጣጣሚነት በሙዚቃ ጣዕም የመለከፋቸውን ልክ አንሮታል። ሙዚቃን "የስሜት መግለጫ ቋንቋዬ፤ የሀዘንና ደስታዬ ጓድ” ይሉታል-የኋላዋ እማሆይ ጽጌማርያም፤ የያኔዋ የውብዳር ገብሩ! እማሆይ ጽጌማርያም ውልደታቸው ከደህና ቤተሰብ መደብ ነው። አባታቸው ከንቲባ ገብሩ ደስታ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ጉልህ አሻራ አላቸው። ዕውቁ የታሪክ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ከንቲባ ገብሩ ደስታን ከ20ኛው ከፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት ፋናወጊዎች መካከል አንዱ ናቸው ይሏቸዋል። በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግስት በጣና ሐይቅ ምዕራባዊ ዳርቻ አለፋ ጣቁሳ የተወለዱት ገብሩ ደስታ ገና በልጅነታቸው በሚሲዮናዊያን ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ተወስደው የተማሩ፤ በተለያዩ ሀገራት ተዘዋውረው ያስተማሩና በኋላም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው ከአጼ ዮሐንስ እስከ አጼ ኅይለስላሴ ዘመነ መንግስት ሀገራችውን ያገለገሉ ጎምቱ ባለታሪክ ናቸው። ከንቲባ ገብሩ ደስታ የሀረር እና የጎንደር ከንቲባ፤ በአሜሪካና በአውሮፓ ሀገራት የዲፕሎማቲክ ልዑክ መሪ፣ የመጀመሪያው ሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ በኋላም ዋና አፈ ጉባዔ ነበሩ። ከንቲባ ደስታ በየዘርፋቸው ኢትዮጵያን ያገለገሉ ልጆችን በእግራቸው ተክተዋል። ኮሎኔል ዳዊት ገብሩ፣ ገነት ገብሩ፣ ደስታ ገብሩ፣ የውብዳር ገብሩና ስንዱ ገብሩ ተጠቃሽ ናቸው። የውብዳርም የሕይወት ውጣውረድና አቀበት አልፈው፤ መክሊታቸውን ፈልገው የኖሩ ተምሳሌታዊ መናኒት ሆነዋል። ልደታቸው ታኅሣሥ 13 ቀን 1916 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ነበር። ገና በ6 ዓመታቸው በኋላ የጦር አርበኛ፣ ፀሐፊ ተውኔት፣ ደራሲ፣ የመጀመሪያዋ ሴት የፓርላማ ተመራጭና ዲፕሎማት ከነበሩት ታላቅ እህታቸው ስንዱ ገብሩ ጋር ስዊዘርላድ ለትምህርት አቀኑ። የውብዳር ወደ የባሕር ማዶ ጉዟቸውን ሲያስታውሱ "ከጅቡቲ ጉዞ በጀመርንበት ጀልባ ላይ የተሳፈርን ብቸኛዎቹ ጥቁሮች እኛ ነበርን። በዚያ ድቅድቅ ጨለማ ሰማዩ ላይ የፈካችውን ሙሉ ጨረቃና ማዕበል የሚንጠውን ባህር በተመስጦ ነበር የምመለከተው። ከዚያ በመነሳት በኋላ ላይ “የባህር ላይ ዘፈን- Song of the sea' የሚለውን ሙዚቃ ደረስኩ" ብለው ነበር። የተፈጥሮን ውበት ልክ በሙዚቃ ኅይል በመግለጥ የተካኑ ጠቢብ ናቸውና ገጠመኛቸውን በረቂቅ ሙዚቃ ተራቀቁበት። በስዊዘርላንድ 'ሞንትሚሬል ትምህርት ቤት' በዕድሜ ትንሿ ተማሪ ነበሩ። አንድ ዕለት የቫዮሊን ድምፅ ሰምተው ተማረኩና መጫወት ጓጉ። በሌላ ዕለት አንዲት ፒያኖ አግኝተው ቁልፉን በጣቶቻቸው እየደቆሱ ምስቅልቅል ስሜታቸውን አስተጋቡበት። ሙዚቃውንም 'ማዕበል' ብለውታል። እናም ከቀለም ትምህርቱ በተጓዳኝ ቫዮሊንና ፒያኖ አጠኑ።ገና በ10ኛ ዓመታቸው የመጀመሪያ የሙዚቃ ትርዒት አቀረቡ። “ከንቲባ ገብሩ የኢትዮጵያ ባለውለታ” በተሰኘው የወንድማቸው ኮሎኔል ዳዊት ገብሩ መጽሃፍ ውስጥ የተጠቀሰው የእማሆይ ጽጌማርያም ማስታወሻ "... በሰባት እና በስምንት ዓመት ዕድሜዬ፣… ከሥነ ፍጥረት ጋር ወዳጅነት ነበረኝ፡፡ አበቦች ውብ ልዕልቶች፣ ዛፎች… እንደ ዘበኞቻቸው፣ ነፋስ… ወጣት መልዕክተኛ፣ ፀሐይ… ደግሞ የዓለም ኹሉ ንግሥት ኾነው ይታዩኝ ነበር፡፡ ያን ጊዜ በአዳሪ ትምህርት ቤቱ ውስጥ በኔ ዕድሜ ልጅ ስላልነበረ…ብቸኝነት የሕጻንነት ጓደኛዬ ኾኖ አብሮኝ አደገ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አንድ የኀዘን ስሜት፣ የመንፈስ ዕረፍት ዕጦት አደረብኝ፡፡ ሙዚቃ እወድ ነበርና ስሰማው የኀዘን ስሜት ያመጣብኝ ነበር" ይላል። የፒያኖ ትምህርታቸውን አዲስ አበባ ተመልሰው በእቴጌ መነን አዳሪ ትምህርት ቤት አጠናክረዋል። ልምምዳቸው ግን በጣሊያን ወረራ ምክንያት ተቋረጠ። የ13 ዓመት ልጃገረድ ነበሩ። በፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ከነቤተሰቦቻቸው በፖለቲካ እስረኛነት ወደ ኢጣሊያ አሲናራ ደሴት ወህኒ ቤት ተጋዙ። በግዞት ሆነው ግን ከካቶሊክ ሲስተሮች ጋር ኦርጋን ይጫወቱ ነበር። ሙዚቃ ልክፍታቸው ነውና!! ከሶስት ዓመት ግዞት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ቢመለሱም የሙዚቃ ቃና ልክፍታቸው ግን ወደ ውጭ ሀገር ተመልሶ የመማር ጉጉታቸው ናረ። እናም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጸሃፊነት ስራቸውን አቋርጠው የትምህርት ዕድል ተፈቅዶላቸው ወደ ግብጽ ካይሮ አመሩ። በካይሮ ቆይታቸው “ቬሉኑስ ኮንሰርቫቶሪ ኦፍ ሉቺኒያ” በተሰኘ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ቫዮሊንና ፒያኖ ተምረው ዲፕሎማ ተቀበሉ። "በየዕለቱ ቫዮሊን ለአራት ሰዓታት፤ ፒያኖ ደግሞ ለአምስት ሰዓታት ያህል እጫወታለሁ። በየመሃሉ ደግሞ ወደ ሬስቶራቶችና ፊልም ቤቶች እየሄድኩ እዝናና ነበር" ብለዋል በአንድ ወቅት ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ። በካይሮ ሙቀት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ እስኪመለሱ ድረስ የሙዚቃ ናፍቆታቸውን በቅጡ አጣጠመዋል። የውብዳር የሙዚቃ ጥማቸውን አልቆረጡም። አውሮፓ ተሻግሮ የመማር ፍላጎታቸው አልተቋረጠም። በእንግሊዝ ነፃ የሁለት ዓመት የትምህርት ዕድል ቢያገኙም ሳይፈቀድላቸው ቀረ። ክፉኛ አዘኑ። ከከባድ ህመምና ድባቴም በህክምና ዳኑ። በሂደትም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውብ ዝማሬዎች እየተሳቡ መጡ። የሙዚቃ ትምህርት ምናኔያቸው ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ምናኔ ተለወጠ። ውሎ አዳራቸው ቤተ መቅደስ ሆነ። ".... የዚህ ዓለም ፍቅር እና የመኖር ፍላጎት ከኅሊናዬ ፈጽሞ ተወገደ" ብለዋል በማስታወሻቸው። ከ'የውብዳር ወደ 'እማሆይነት' ምናኔ በወቅቱ የ19 ዓመት ልጅ ነበሩ። በአንድ ዕለት ወጣቷ የውብዳር ለንግስ በዓል ከአዲስ አበባ ወሎ ግሸን ማርያም ተጓዙ። ለሁለት ዓመታት ሰዓታትና ቅዳሴ ሳያቋርጡ ተማሩ፤ ፀለዩ። ታሪክን እንዲህ ያወሳሉ። “…ሁሉንም ነገር ዕርግፍ አድርጌ ትቼ ከዓለም ተነጠልኩ። እቅዴ በጫካ ውስጥ ባህታዊ ሆኜ ኑሮን ለመግፋት ነበር። ግሸን ማርያም እንደደረስን መነኮሳቱን ቀሳውስቱንና አቡነ ሚካኤልን አገኘሁ። ለመመንኮስ እንደመጣሁ ለአቡነ ሚካኤል ነገርኳቸው። እርሳቸው ግን ፈቃደኛ አልነበሩም። እኔም ውሳኔዬ መሆኑን አስረግጬ ነገርኳቸው.... በሀሳቤ የፀናው መሆኑን ካረጋገጡ በኋላ ተስማሙ" ይላሉ። እናም መስከረም 21 ቀን 1940 ዓ.ም. በ20ዎቹ ዕድሜያቸው መጀመሪያ ለማዕረገ ምንኩስና በቁ። 'የውብዳር' የተሰኘው ስማቸው በክርስትና ስማችው እማሆይ ጽጌማርያም ተቀየረ። እማሆይ ሙሉ ጊዜያቸውን ለሙዚቃ ቅማሬ እና መንፈሳዊው ግልጋሎት ሰጡ። "... ሙዚቃውን እንዳላጣው ፈለገ። ሁሉም በእርሱ ሞገስ ነው የሆነው" ይላሉ። ለአስር ዓመታት በግሸን ማርያም ገዳም ያለ ጫማ ተጉዘዋል። እማሆይ ፅጌማርያም በመንፈሳዊ ሕይወትም፤ በረቂቅ ሙዚቃም መንነዋል። የሙዚቃ ስራዎቻችውም ከአፍሪቃ ቀንድ አልፎ በምዕራቡ ዓለም ናኝቷል። ስራዎቻቸውም ታዲያ ከመንፈሳዊ ተመስጦ ባሻገር ለሰብዓዊ ርዳታ ተልዕኮ የሚውል ነበር። እማሆይ ጽጌማርያም ከመጀመሪያ አልበማቸው ጀምሮ ከአልበም ሽያጭ የተገኘ ገቢ ለግላቸው ተጠቅመው እንደማያውቁ ይነገራል፤ ለህጻናት እርዳታ ያውላሉ እንጂ። “በደርግ ዘመን ከታተመው አራተኛ አልበሜ ያገኘሁትን ገንዘብም ኢየሩሳሌም ውስጥ ያለችውን የኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ለመደገፍ አዋልኩት። ዘቪዥነር ከተሰኘው አልበሜ ያገኘሁትን ገንዘብም በወቅቱ የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ከወዲያ ወዲህ ይል ለነበረው ኢጂኤም ፋውንዴሽን ድጋፍ አድርጌበታለሁ። ሶቨኔርስ የተሰኘ ስድስተኛ አልበሜ የተገኘው ገቢም በኢየሩሳሌም ለሚገኝ ቤተክርስቲያን ድጋፍ የሚውል ነው” ብለዋል እማሆይ። ሙዚቃ በሸክላ ለማስቀረጽ የወሰኑትም በጎንደር በነበሩበት ወቅት ከቅዳሴ መልስ ባጋጠማችው ክስተት እንደነበር እንደህ አውስተዋል። "ጎንደር በነበርኩበት ጊዜ በየቤተክርስቲያኑ የማይጠገበውን ማኅሌት ሰምቼ ስመለስ፤ እደጅ የአገር ቤት ተማሪዎች በየሜዳው ጥቅልል ብለው ተኝተው አያለሁ፡፡ ብጠይቅ ሌሊት ቤተክስቲያን ያደሩ ናቸው፣ ቤት የሌላቸው፡፡ በዚህም ልቤ ተነካ፣ አዘንኩ፡፡ እኔ ሀብት የለኝ፤ ያለችኝ ያቺው ሙዚቃዬ፡፡ ስለዚህ እስኪ ሙዚቃዬን ላስቀርጽ እና ሽያጩን እነዚህ ልጆች ገብተው በነጻ የሚያድሩበት ቤት ላቋቁም አልኩ" ይላሉ። እማሆይ ጽጌማርያም እስከ ሕልፈተ ሕይወታቸው ድረስ ለአራት አስርት ዓመታት ገዳማ ኑሯቸውን በሀገረ-እስራኤል ኢየሩሳሌም በሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት አድርገው ቆይተዋል። 'የፒያኖዋ እመቤት' ረቂቅ አሻራዎች እማሆይ ጽጌማርያም የአንድ ምዕተ ዓመት ምድራዊ ሕይወት ዘላለማዊ አይረሴ ስራዎች አቅርበዋል። በፒያኖ ረቂቅ ሙዚቃ ቅማሬያቸውም 'የፒያኖዋ እመቤት' የሚል ስም አትርፈዋል። እማሆይ ጽጌማርያም ከዓለማዊ ወደ መንፈሳዊ ሕይወትን የዘነቁ፣ ሀገርኛ ወደ ባህር ማዶ ረቂቅ ጥበብን አዋህደው የተራቀቁ፣ የፒያኖ ቀማሪ፣ የቫይሊን ደርዳሪ፣ የኖታቸው ቃና መንፈስን ኮርኳሪ፣ ስክነትና ጥልቅ ተመስጦን መካሪ፣ መክሊታቸውን የኖሩ፣ በስራዎቻቸው አድማስ ዘለል አድናቆትና ሞገስ የተቸሩ፣ ... የረቂቅ ሙዚቃ እመቤት ናቸው። የኢትዮጵያን ሙዚቃ ለመጀመሪያ ጊዜ በጀርመን ሀገር በሸክላ ካስቀረጹት ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ቀጥሎ እማሆይ ፅጌ ማርያምም የኢትዮጵያን ክላሲካል ሙዚቃዎች በሲዲ በማስቀረፅ ለዓለም ሕብረተሰብ ያስተዋወቁ የመጀመሪያዋ እንስት ናቸው። በአጠቃላይ ስድስት የሙዚቃ አልበሞችን አሳትመዋል። በ1955 ዓ.ም. “ሆምለስ ወንደረር-ቤት አልባ መንገደኛ” እና “ሶንግ ኦፍ ዘ ሲ-የባሕሩ ዜማ” ሁለት አልበሞች ጀርመን ውስጥ አስቀርጸዋል። ዕውቁ የሙዚቃ ሊቅ ሞዛርት በተጫወተበት ፒያኖ የመጫወት ዕድል ገጥሟቸዋል። የቤቶቨንን፣ የሞዛርትንና ሽትራውዝን ጨምሮ የአያሌ ክላሲካል ሙዚቃ ሊቆችን ስራዎች ተጫውተዋል። ከ1950ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን አቅርበዋል። በኢየሩሳሌም ሁለት ኮንሰርቶች አቅርበዋል። ስራዎቻቸው 'ኢትዮፒክስ' በተሰኘው የፈረንሳዊው አቀናባሪ ፍራንሲስ ፋልሴቶ ተከታታይ የሙዚቃ አልበሞች ውስጥ ተካተዋል። የእማሆይ ጽጌማርያም ሙዚቃ 'ፓሲንግ' የተሰኘው የሆሊውድ ፊልም እና የፔጆ መኪና ማስታወቂያን አጅቧል። እማሆይ ስራዎቻቸውና ስብዕናቸውም የተጣጣመ ነው። በ1950 ኮንሰርታቸው በወሎ ረሀብ አደጋ ተጎጂ ዜጎች ድጋፍ ለማሰባሰብ ታልሞ በተዘጋጀው ኮንሰርት ላይ የቬትሆንን 'ፓቲክ' እና 'ሆምለስ ወንደረር' የተሰኘ ስራዎች ተጫውተዋል። ወደ ወሎ ሂደው በርሀብ አለንጋ የተገረፉ ህጻናትን በአካል በማየት ‘የድርቅ እልቂት-famine disaster' የተሰኘ ሙዚቃ ደርሰዋል። የፒያኖዋን እመቤት ሥራዎች ለቀጣይ ትውልድ ለመዘከር የተቋቋመው 'የእማሆይ ጽጌማርያም ፋውንዴሽን' በረቂቅ የሙዚቃ ዘርፍ ዕድገት የበኩሉን ሚና ሲጫወት ቆይቷል። በእማሆይ የሙዚቃ መንበር ለመቀመጥና ለረቂቅ ሙዚቃ መራቀቅ የሚሹ ወጣቶችን ይደግፋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እና በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር በሚገኘው የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ፒያኖን ጨምሮ ለሙዚቃው እምርታ የሚያግዝ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። ለዓመታት ሲገለገሉበት የነበረው ፒያኖም ለያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እንዲሰጥ በመናዘዛቸው በቅርቡ ለትምህር ቤቱ ተሰጥቷል። ከሕልፈተ ሕይወታቸው በኋላ “ኢየሩሳሌም” የተሰኘ 10 የፒያኖ ትራኮች የያዘ አልበማቸው በሚሲሲፒ ሪከርድስ አማካኝነት እንደሚወጣ ተገልጿል። እማሆይን የሚዘክሩ መፃሕፍት በተለያዩ ወገኖች ታተመዋል፤ ጥናትና ምርምር ስራዎችም እየተሰሩ ነው። እማሆይ በሙዚቃ ጠበብቶች ሲዘከሩ... እማሆይ አራቱን የኢትዮጵያ ቅኝቶች በአንድ ድርሰት በመቀመማቸው የሙዚቃ ጠበብት ያደንቋቸዋል። ከሰሞኑ "የፒያኖዋ እመቤት" እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ በሕይወት ዘመናቸው ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ኢንዱስትሪ ዕድገት የነበራቸውን አበርክቶ የሚዘክር መርሐግብር በእንጦጦ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ ሲካሄድ በርካታ ታዋቂ ሰዎችና የኪነ ጥበብ ሰዎች ታድመው ነበር። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እማሆይ ጽጌማርያም በጠላት ወረራ የአርበኝነት ዘመን ክፉውን ጊዜ የቀመሱ፣ ሕይወታቸውም አልጋ ባልጋ ሳይሆን በውጣ ውረድ የተሞላ፣ በሀገር አንድነትና በኅይማኖት በጽኑ የሚያምኑ እንደሆኑ ገልጸዋል። "የሙዚቃ ስራዎቻቸው ፍትህን፣ አንድነትን፣ መንፈሳዊነትን እና ሰላምን የሚገልጹ ናቸው። የእማሆይ የሙዚቃ ስራ በተጨነቅን ጊዜ ስናደምጥው መንፈስ የሚያረጋጋ ሕያው ስራ ነው፤ ተማሪዎች ፈለጋቸውን እንደሚከተሉ ተስፋ አደርጋለሁ" ሲሉ ተደምጠዋል። የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሰብሳቢ አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ "የእማሆይ ጽጌማርያም ስራ በወረቀት ተጽፎ የሚቀር ሳይሆን በልብና በአዕምሯችን ታትሞ የሚቀር ነው" ሲሉ ገልጸውታል። በረቂቅ ሙዚቃ አጨዋውታቸው ዓለምን ያስደነቁ፤ የህያው ስራ ባለቤት እንደሆኑም እንዲሁ። በእንጦጦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሙዚቃ ባለሙያው በላይ አለማየሁ እማሆይ ጽጌማርያም "ዘመናዊ ሙዚቃ ባልተለመደበት ዘመን አዲስ የሙዚቃ ስነ ዘዴ ያመጡ፤ የሙዚቃ ስራዎቻቸውም ኢትዮጵያዊውን ቃና ከአውሮፓ ሙዚቃ በማዋሀድ በሁለት ቅኝቶች ውህደት አዲስ ፈጠራ ያመጡ፣ የሙዚቃ ዕውቀታቸው የሚያስደንቅ፣ ዋጋ ከፍሎ ህልምና ማሳካት እንደሚቻል በሙዚቃ ልህቀት ላይ በመድረስ በተግባር ያሳዩ የጥበብ ሰው፣ ለሙዚቃው ዘርፍ ተግባራዊ ምሳሌ ናቸው" በማለት ይገልጸዋቸዋል። የሙዚቃ ትምህርት ክፍል አሰልጣኟ ዊንታና ንጉሴ በበኩሏ "እማሆይ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ትልቅ ሚና የተጫወቱ ስራዎቻቸውም የሚዘከሩ ናቸው፤ እንደ ሙዚቃ መምህርነቴም አርዓያዬ ናቸው" ትላለች። በእማሆይ ጽጌማርያም ስራዎች ላይ የመመረቂያ ስራዋን ያዘጋጀቸው ሰዓሊና ዲዛይነር ሀበሪ እጅጉ በበኩሏ "እማሆይ ምድራዊና ሰማያዊ ሕይወት አቻችለው የኖሩ፤ ሁለት ድል ያሳዩ ናቸው። ጥቁር ኢትዮጵያዊ ሆነው በዓለም የታወቁ፣ ለዓላማችው ስኬት ትልቅ ተጋድሎ ያደረጉ፣ በመክሊት መኖርን የሚያስተምሩ እናት" ትላቸዋለች። የኢትዮ ጃዝ አባት የሚሰኘው አንጋፋው ሙዚቀኛ ሙላቱ አስታጥቄ ከወራት በፊት ለቢቢሲ በሰጠው ቃለ መጠይቅ "እማሆይ በእውነት እጅግ የማደንቃቸው እና የማከብራቸው ታላቅ ባለሞያም፤ ታላቅ ሰው ናቸው። ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል.... የእማሆይ ጽጌ ማርያም ሥራ ተጠንቶ በየትምህርት ቤቱ እንዲቀመጥ፣ እንዲጠና ማድረግ የግድ አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁ። የሙዚቃ ትምህርት ካሪኩለም ውስጥ እንዲገባ እና ወጣቶቹ እንዲማሩት ማድረግ ያስፈልጋል" ይላል። ዕውቁ የሙዚቃ ባለሙያ ሃያሲ ሰርፀ ፍሬስብሃት በአንድ ወቅት በፃፈው መጣጠፍ እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ በክላሲካል ሙዚቃ ዘርፍ በብቸኛ የሙዚቃ ቀማሪነት እና ፒያኒስትነት ጉልህ የታሪክ ቦታ እንደያዙ ገልጿል። "እማሆይ ጽጌ ማርያም በሙዚቃ ምክንያት ብዙ ተፈትነዋል፡፡ ከመንፈሳዊ ሕይታቸው ጋር የሚቃረን የሚመስላቸው አንዳንዶች፣ ሙያቸውን እና የሙዚቃ ፍቅራቸውን አጣጥለውባቸዋል፡፡ የሕይወታቸውን አቅጣጫ ፍጹም በማይገመት መንገድ እንዲጓዝ ያደረገም ነው፡፡ ከሀገራቸው አሰድዶ ተነጥለው እንዲኖሩ ያደረገ ነው፡፡ ግን ከዚህ ኹሉ በኋላ የስማቸው ትንሣኤ፣ ከዘጠኝ ዐሥርት ዓመታት በኋላ በታላቅ ክብር ለብዙዎች ታይቷል" ብሏል፡፡ እማሆይ ራሳቸውም "አንዳንድ ሰዎች ይቃወሙታል። ነገር ግን ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው የሚሆነው። ይሄ የክላሲካል ሙዚቃ ነው። እግዚአብሔርንም በተለያዩ የሙዚቃ መሳሪያዎች ማወደስ ይቻላል" ሲሉ ለቢቢሲ ራዲዮ ፎር ተናግረዋል። ሰሞን ታዋቂው ጋዜጣ ኒወርክ ታይምስ "ባለልዩ ተስጥኦ ኢትዮጵያዊ መነኩሲት" በሚል ሰፊ ሀተታ ጽፏል። በዚሁ ጋዜጣ ላይ ኖራ ጆንስ የተባለ ሙዚቀኛ "የእማሆይ አልበም እስካሁን ከሰማኋቸው ውብ ሙዚቃዎች ሁሉ የላቀ ስራ ነው" ሲል አድንቆታል። እስራኤላዊት ሙዚቀኛ ማያ ዱኔትዝ እማሆይ "የምዕራቡን ዓለም ረቂቅ ሙዚቃ ከኢትዮጵያዊ ባህላዊ ሙዚቃ ቅርስ ጋር በመቀመር ለዓለም ጆሮ አዲስ ድምጽ አፍልቀዋል። …ሙዚቃዎቻቸው በስፋት መንፈሳዊ መልክ አላቸው። የእማሆይ ሙዚቃዎች የጥሞና፣ ትህትና፣ የጥልቅ ተመስጦ፣ የሰላማዊ ድባብ፣ አሳዛኝ ግን በፍቅርና በእምነት የተዋጡ ... ድምጾች" በሚል ትገልጻቸዋለች። እማሆይ ጽጌማርያም የሙዚቃ ኅይል በርግጥም ውስጥን የሚፈነቅል፤ መንፈስን የሚሰረስር መሆኑን በዘመናቸው ሁሉ ከሙዚቃ ጋር ላይነጣጠል ከህይወታቸው የተጋመደ በሰሯቸው ዘመን አይሽሬ ስራዎች አሳይተውናል። የእማሆይ ጽጌማርያም የአንድ ምዕተ ዓመት ምድራዊ ሕይወት ዘላለማዊ አይረሴ ስራዎች በትውልዱ ውስጥ እንደረቀቁ ይኖራሉ።
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች
May 26, 2023 300
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች ሰለሞን ተሰራ አውሮፓዊያን ለጥቁሮች ከነበራቸው ዝቅተኛ አመለካከት በመነጨ እብሪት “የአፍሪካ ቅርምት” እየተባለ በሚታወቀው አጀንዳቸው አህጉሪቱን ለመከፋፈል ቁጭ ብለው የመከሩት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ማገባደጃ ላይ ነበር፡፡ በጀርመን መዲና በርሊን የተሰበሰቡት ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ፖርቱጋል፣ ቤልጂየም እንዲሁም ዘግይተው የተቀላቀሉት ጣልያን እና ጀርመን አቅማቸው የፈቀደውን ያህል አህጉሪቱን በመቆጣጠር ሀብቷን ለመመዝበር ሕልም አንግበው የወል ቃል ገብተዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት አፍሪካን አንድ አድርጎ ለመግዛት ሕልማቸውን አስተሳስረው ቢነሱም በመሀከላቸው በነበረው ፉክክር የተነሳ ምኞታቸው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ አውሮፓውያን በአህጉሪቱ የዘረጉትን የቅኝ አገዛዝ መዋቅር በጣጥሶ ለመጣል በቅድሚያ አህጉሪቱን አንድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን የሚያምኑ አፍሪካውያን መሪዎች ህብረት ለመመስረት ቢነሱም ሀሳባቸው ለሁለት በመከፈሉ ሁለት ቡድን እንዲፈጠር ምክንያት ሆኖ አልፏል፡፡ ይህን ተከትሎ የተፈጠሩት ሁለት ቡድኖች በአንድ ወገን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ሀገራቱ በፍጥነት ተዋሕደው አፍሪካ አንድ ልትሆን ይገባል የሚለው የካዛብላንካ ቡድን፤ እንዲሁም አንድ ከመሆን በፊት ሌሎች ትብብሮች ሊቀድሙ ይገባል የሚለው የሞኖሮቪያ ቡድኖች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ቡድኖች የአፍሪካ አንድነት እንዲመሰረት ጽኑ አቋም ቢኖራቸውም፣ እንዴት ነው መመስረት ያለበት የሚለው ጥያቄ ግን የልዩነታቸው ወሰን ሆኖ ወደ ንትርክ የገቡበት ጊዜ ነበር። በ1961 የተመሰረተው የካዛብላንካው ቡድን በጋናዊው ኩዋሜ ኑኩርማህ የሚመራ ሲሆን ዓላማቸው አፍሪካ አሁን መዋሃድ (አንድ መሆን) አለባት የሚል ሲሆን ከአባላቱ መካከል ጊኒ፣ ሊቢያ፣ ግብጽ፣ ሞሮኮ፣ ማሊ፣ አልጄሪያ ይገኙበታል። የሞኖሮቪያው ቡድን ደግሞ በሴኔጋላዊው መሪ ሴንጎር የሚመራ ሲሆን በስሩም ሃያ አራት ሃገራትን፣ ማለትም ናይጄሪያ፣ ሴኔጋል፣ ካሜሮን፣ አይቮሪኮስት፣ ቶጎ፣ ላይቤሪያ እና ሌሎች ብዙ የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበሩ ሃገራትን ያቀፈ ነበር፡፡ የዚህ ቡድን የውህደት መርህ ደግሞ “አፍሪካ መዋሃድ የምትችለው በኢኮኖሚያዊ ትብብር ሆኖ በቀስታ በምታደርገው ጉዞ ነው” የሚል ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ወገኖች ፍጥጫ አርግባ ወደ ውህደት ያመጣቻቸው ኢትዮጵያ ስትሆን ድርጅቱ የዛሬ 60 ዓመት እ.ኤ.አ ግንቦት 25 ቀን 1963 ሲመሰረት የመጀመሪያው ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አጼ ኃይለስላሴ ነበሩ፡፡ የፓን አፍሪካኒዝም ልጅ የሆነው የያኔው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋና ዋና ዓላማዎቹ ቅኝ ገዢዎችን ማስወገድ፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል አንድነትና ሕብረትን ማበረታታት፣ ለአፍሪካዊያን የተሻለ ህይዎት እና እድገት ለማምጣት፣ ሉዓላዊነትንና የወሰን አንድነትን ማስጠበቅ፣ ሰብዓዊ መብቶችን ማስከበር፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል የሚካሄዱትን ግጭቶች በሰላማዊና በዲፕሎማሲ መፍታት የሚሉ ነበሩ። የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀደምት መሪዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን የሚተካ አዲስ አህጉራዊ ድርጅት ለመመስረት እ.አ.አ በ1999 ያሳለፉትን ውሳኔ መሠረት በማድረግ የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ በሐምሌ 2002 በደርባን ደቡብ አፍሪካ በይፋ መመስረቱ ይታወቃል። የአፍሪካ ኅብረት ራዕይም፤ የተቀናጀች፣ የበለጸገች እና ሰላማዊ፣ በራሷ ዜጎች የምትመራ እና በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ተፎካካሪ የሆነች አፍሪካን መመስረት ነው። እ.አ.አ በ2013 የአፍሪካ መሪዎች በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት አጀንዳ 2063 የተሰኘውን አህጉራዊ እቅድ ነድፈዋል። እቅዱ ከሁሉም በላይ በአህጉሪቱ ላይ የሚቃጡ ጦርነቶችን ማስቆምና መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላይ የሚያተኩር ሲሆን በአህጉሪቱ ዜጎች ከአገር አገር ነፃ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ራዕይ የሰነቀ ነው። ሌላው ወሳኝ ፕሮጀክት የአፍሪካ ነፃ ገበያ ምህዳርን መክፈት ሲሆን ይህ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ በርካታ አገራትን አሳታፊ በማድረግ የዓለም ትልቁ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ ስምምነት ሲሆን አሁን ላይ ተግባራዊ ሊደረግ ከጫፍ ደርሷል። ይህ የነፃ ገበያ ስምምነት በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ለማስፋፋት የታለመ ከመሆኑ በላይ የሀገራቱን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድገው ታምኖበታል። የአፍሪካ ነፃ ገበያ ስምምነት አገራት የውስጥ ገበያቸውን ለመጠበቅ ባወጧቸው ቀደምት ህጎችና እንዲሁም በደካማ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ምክንያት ከፍተኛ ችግር እንደሚገጥመው አስተያየት ቢሰጥበትም ያዘለው ተስፋ ግን ከችግሩ የገዘፈ ነው። ሁሉንም የአፍሪካ አገራት መዲናዎች እና የንግድ ማዕከሎች በፈጣን የባቡር መስመር ማገናኘት፣ በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ማበረታታት እንዲሁም የአፍሪካ አገራት በዓለም አቀፍ የንግድ ገበያ ያላቸውን ተሳትፎ ማጎልበት አጀንዳ 2063 ካስቀመጣቸው ግቦች መካከል ቀዳሚዎቹ ናቸው። አፍሪካውያን በአህጉሪቱ በነፃነት የመዘዋወር፣ የመስራት እና የመኖር መብት እንዲኖራቸው ማድረግ እንዲሁም በአህጉሪቱ ያሉ ግጭቶችን ማስቆም እና ሌሎችም በርካታ ግቦች በእቅዱ ላይ ተቀምጠዋል። ነገር ግን የአፍሪካ ሕብረት እነዚህን አጀንዳዎች ለማስፈፀም በእጅጉ እየተፈተነ ሲሆን ለዚህ ዋነኛ መንስኤው የሕብረቱ አባል አገራት በገቡት ስምምነት መሰረት ነገሮችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ማስገደድ አለመቻሉ እንደሆነ ይነገራል። ተንታኞች እንደሚሉት የአፍሪካ አገራት ያለባቸውን ከፍተኛ የእዳ ጫና ለመክፈል የሚያደርጉት ትግል ትልቁን አህጉራዊ አጀንዳ ችላ እንዲሉ ግድ ብሏቸዋል። የህብረቱ በጎ ርምጃዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋነኛ ዓላማው በቅኝ አገዛዝ ስር የነበሩ ሀገሮችን ነጻ ማውጣት ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር የተሳካ ተግባር ማከናወኑ በታሪክ ሲወደስለት የሚኖር ስኬቱ ነው፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆኖ ከሞላ ጎደል ውጤት ያስመዘገበባቸው ዘርፎች አሉ። ሀ. ሰላምና ደህንነት የአፍሪካ ህብረት ሰላምንና ደህንነትን ለማረጋገጥ በተለይም የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ኃይል በተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች ያደረገው ተጋድሎ በአዎንታ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ለማሳያም ላይቤሪያ፣ ሴራሊዮን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን ተሰማርቶ የነበረው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ኃይል ከሌሎች የተሻለ አፈጻጸም እንዳለው ይገለጻል፡፡ ለ. ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በተለያዩ የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መረጋጋት እንዲፈጠር ለማድረግና ዴሞክራሲን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት እና የተፈጥሮ ሃብቷ ለፈጣን ዕድገቱ በምክንያትነት ይነሳሉ፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋና ኢኮኖሚው እንዲያድግ የወሰዳቸው ተቋማዊ እርምጃዎች ወሳኝ ሚና ሲኖራቸው የአፍሪካ ልማት ባንክን በማቋቋም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መደገፉ ተጠቃሽ ነው፡፡ በተለይም ለመንገድና ለውኃ ሃይል ማመንጫ ባንኩ ያደረገው ድጋፍ ተገቢው ቦታ የሚሰጠው ሲሆን ለአፍሪካ የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነት መሻሻል ማነቆ የሆኑትን ታሪፍ በመቀነስም የተሻለ ስራ ሰርቷል፡፡ ሐ. ዓለም አቀፍ ተሰሚነት የአፍሪካ ህብረት በዓለም አቀፍ መድረኮች በተለይም የዓለም ኢኮኖሚንና የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከተ አንድ አቋም መያዙ ከህብረቱ ታሪክ ተጠቃሽ ስኬቶች አንዱ ነው፡፡ አፍሪካ የአየር ንብረት ተፅዕኖውን ለመላመድና ለመቋቋም የሚረዳትን ተገቢውን ክፍያ እንድታገኝ ህብረቱ ውጤታማ ስራ ሰርቷል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ የልማት ችግሮችን ለመፍታት ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ጥረት አድርጎ ባስመዘገበው ውጤትም ይመሰገናል፡፡ በተለይም የተባበሩት መንግስታት የሚሊኒየም የልማት ግቦች እንደ መገለጫ ይነሳሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ለማግኘት እንዲሁም የአፍሪካ ድምጽ የሚጎላበት ሚዲያ እንዲኖር የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች በአዎንታ የሚነሱ ናቸው። መ. ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ ዴሞክራሲንና መልካም አስተዳደርን በማስፈን በኩልም ከነጉድለቶቹም ቢሆን በመልካምነት የሚጠቀሱ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይገለጻል፡፡ በአህጉሪቷ ከ30 ዓመት በፊት አምስት ሀገራት ብቻ ዴሞክራት የነበሩ ሲሆን አሁን ከአፍሪካ ሀገሮች 95 በመቶዎቹ ወቅቱን ጠብቀው ምርጫ የሚያካሂዱ ሀገራት ናቸው፡፡ የምርጫ ታዛቢዎችን በአባል ሀገራት እየላከ መታዘቡም እንደ ጥሩ ጅምር መታየት ያለበት ነው፡፡ በተለይ ደግሞ የአፍሪካ የእርስ በርስ መገማገሚያ መድረክን /APRM/ ማቋቋሙ በጥንካሬ ሲነሳ በዚህ መድረክ አማካኝነት ሀገራት በራሳቸው ተነሳሽነት ስለሀገራቸው የመልካም አስተዳደር አፈጻጻም ሪፖርት የሚያደርጉበትና ልምድ የሚለዋወጡበት እድል ተፈጥሯል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በሀገሮች ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ያለመግባት መርህ በማሻሻል በመፈንቅለ መንግስት የሚመጡ ቡድኖችን ላለመቀበል መወሰኑ ህብረቱ በዴሞክራሲ ላይ ያለውን አቋም ያሳያል፡፡ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች በርግጥ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት አንግቦት ከነበረው አባል ሀገራቱን ከቅኝ ገዥዎች ነፃ የማውጣት ተልዕኮ አንስቶ እስከ ወቅታዊው የአየር ንብረት ለውጥ ድርድር አበጀህ የሚያስብሉትን ስኬቶች አስመዝግቧል፡፡ በቀዝቃዛው የዓለም ጦርነት ጊዜ አብዛኛው ሃገራት የገለልተኛ ሀገሮች ማህበር አባል ቢሆኑም የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርሳቸው ተከፋፍለው አፍሪካን የጦርነት አውድማ አድርገዋት ነበር፡፡ አንዱ የአፍሪካ ሀገር የምዕራቡ ካምፕ ደጋፊ ከሆነ ሌላኛው የምስራቅ ካምፕ ደጋፊ ነበር፡፡ ሁለቱም ካምፖች ለርዕዮተ ዓለም ተከታዮቻቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ አፍሪካ እርስ በእርስ እንድትባላ አድርገዋል፡፡ ይህም ህብረቱ የተቀደሰ ሃሳብ ቢኖረውም የማስፈፀም አቅሙ ያን ያህል የተጠናከረ አለመሆኑን ያሳያል፡፡ ለህብረቱ የማስፈጸም አቅም ማነስ አንደኛው ምክንያት ከአባል ሀገራት የሚጠበቀውን ገንዘብ በአግባቡ አለመሰብሰቡ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የህብረቱ የ2023 በጀት 654 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር እንዲሆን በዛምቢያ በተደረገ ጉባኤ ውሳኔ የተላለፈ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 60 በመቶ የሚልቀው በጀት ከለጋሾች እንደሚሰበሰብ በወቅቱ ይፋ ተደርጓል፡፡ በሌላ በኩል አፍሪካ በየዓመቱ 50 ቢሊዮን ዶላር በሙስና እንደምታጣ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ 1 በመቶ እንኳን ማዳን ቢቻል የህብረቱን የ2 ዓመት ወጪ መሸፈን ይቻላል ይላሉ ባለሙያዎች፡፡ ጥቂት በማይባሉ የህብረቱ አባል ሀገራት ሙስና ዛሬም አደጋ መሆኑ፣ የርስ በርስ ግጭት በሚፈለገው ደረጃ አለመፈታቱ፣ ድህነት አሁንም የአህጉሪቱ ቀንደኛ ጠላት መሆኑ፣ የትምህርትና ጤና አገልግሎቶች ተደራሽ አለመሆንና ጥራቱም የተጓደለ መሆን፣ በህብረቱ የሚወሰኑ ውሳኔዎች አፈጻጸም የተለያየና የሚፈለገውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ ውስንነት ያለበት መሆኑ ወዘተ የህብረቱና አባል ሀገራት ጉድለት ሆነው ቀጥለዋል። ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች የአፍሪካ ህብረት ከስኬቱም ሆነ ከልምዱ ለመማር የሚያስችለው ከግማሽ ክፍለ ዘመን የዘለቀ የእድሜ ባለፀጋ ሆኗል፡፡ እናም የወደፊት አቅጣጫውን ሲተልም ያለፈውን ጉዞ ዞር ብሎ ማየት፤ የቆመበትን ነባራዊ ሁኔታ ጠንቅቆ መረዳትና መጭውን አቅርቦ ማሰብ ይጠበቅበታል። ለዚህ ደግሞ የማስፈጸም አቅምን ማጠናከር፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መስጠት፣ ተሳትፎን ማሳደግ፣ የገቢ አቅምን ማሳደግ ወሳኝ ናቸው። ሀ. የማስፈጸም አቅም የአፍረካ ህብረት ከአፍሪካ አንድነት ደርጅት የተሻለ አደረጃጀትና አሰራር እንዳለው የሚቀበሉ አሉ፡፡ ለምሳሌ በሀገሮች ጣልቃ ያለመግባት መርህን በማሻሻል ህብረቱ በመፈንቅለ መንግስት የመጡ ቡድኖችን በአባልነት አይቀበልም ነገር ግን በአፍሪካ አሁንም የእርስ በርስ ግጭት የሚታይባቸው ሀገሮች አሉ፡፡ ስለሆነም ይህንኑ ችግር ሊቀርፍ የሚችልና ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበ አደረጃጀትና አሰራር ሊኖረው ይገባል፡፡ የህብረቱ በጀት በሌሎች አካል መሸፈን አሉታዊ ተፅዕኖ ስለሚኖረው አባል ሃገራት የሚጠበቅባቸውን መዋጮ በወቅቱ በመክፈል የህብረቱን የማስፈፀም አቅም ማሳደግም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለ. የስራ እድል ፈጠራ የአፍሪካ ህብረት በተለይ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ማዕከል ያደረገ እድገትን ማበረታታት ግድ የሚለው ወቅት አሁን ነው፡፡ ሆኖም ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ከማረጋገጥ አኳያ ብዙ የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉ እሙን ነው። በተለይም ወጣቶችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ መሰራት ያለባቸው የቤት ስራዎች በአግባቡ አለመሰራታቸው በጉልህ ይጠቀሳሉ፡፡ እንደ አፍሪካ ኢኮኖሚ አውትሉክ መረጃ በአፍሪካ እድሜያቸው ከ15 እስከ 25 ዓመት ያሉ ወጣቶች ከአህጉሪቱ አጠቃላይ ህዝብ ከ70 ከመቶ በላይ ይሸፍናሉ፡፡ የዓለም ባንክ ያወጣው መረጃ እንደሚያሳየው በአፍሪካ 200 ሚሊዮን የሚጠጉ እድሜአቸው ከ15 እስከ 25 የሚጠጋ ወጣቶች ሲኖሩ ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚጠጉት ስራ ፈላጊ መሆናቸው ደግሞ ህብረቱ የሚጠብቀውን ከባድ ስራ ያሳያል፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በየሃገሮቹ ለወጣቶች ምን ያህል የስራ እድል እንደተፈጠረ መጠየቅን የእርስ በእርስ መገማገሚያ መድረኩ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ ሊያደርገው እንደሚገባ ምሁራን ይመክራሉ፡፡ ሐ. የህዝብ ተሳትፎና የውክልና ዴሞክራሲ ህብረቱ ሊያሳካ ያሰባቸውን ግቦች እውን ማድረግ የሚቻለው በሁሉም የነቃ ተሳትፎ መሆኑ አያጠያይቅም። በመሆኑም አባል አገራት ችግሮችን ከመለየት ጀምሮ እስከ ክትትልና ግምገማ ስርአት ህብረተሰቡን በሁለንተናዊ መርሃ ግብሮች ማሳተፍ ይገባቸዋል፡፡ ይህ ሲደረግ ነው በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ ያሉ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የፈጠራ ችሎታዎችን ማውጣትና ሀገሬ ለእኔ ምን አድርጋለች ሳይሆን እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ የሚሉ ዜጎችን መፍጠር የሚቻለው፡፡ በአፍሪካ በየቦታው የሚታዩ የእርስ በእርስ ግጭቶች መንስኤ በዋነኛነት የህዝብ ፍላጎት አለመሟላት ሲሆን በተለይም የአናሳዎች መብት አለመከበር የግጭት መንስኤ ሲሆን ይታያል፡፡ ለዚህ ደግሞ በየአካባቢው አስተዳደር ህዝቡን በየጊዜው ማማከር ያስፈልጋል፡፡ መ. ውስጣዊ የገቢ አቅምን ማሳደግ በዋናነት አራት የገቢ ምንጮች ያሉ ሲሆን እነሱም የሃገር ውስጥ ብድር፤ ግብርና ታክስ፣ የውጭ ብድር እና እርዳታ ናቸው፡፡ ከግብርና ታክስ በስተቀር ሌሎች የገቢ ምንጮች አሉታዊ ተጽዕኗቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ግብርና ታክስን በአግባቡ መሰብሰብ የአንድ ሀገር የሁለንተናዊ ብቃት መለኪያ ነው፡፡ ግብርና ታክስ የመንግስት ወጪ በመሸፈን ነጻነትን ከማጎናጸፉም በተጨማሪ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍልን ለማረጋገጥ ሁነኛ መሳሪያ ነው፡፡ አልጀዚራ ባወጣው መረጃ መሰረት አፍሪካ በእርዳታና በብድር ከምታገኘው ይልቅ በታክስ ማጭበርበርና ስወራ የምታጣው ከ10 እጥፍ በላይ ይበልጣል፡፡ ለዚህ ደግሞ የታክስ ህጎች ክፍተት መኖርና በሙስና የተጨማለቁ ባለስልጣናት እንዲሁም ብቃት ያለው የሰው ኃይል አለመኖር አስተዋፆኦ ያደርጋሉ፡፡ የገቢ አሰባሰብ ስርአቱን በማሻሻል የአፍሪካን ነጻነት ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአፍሪካን የእርስ በርስ ንግድ ማስፋፋት፤ የታሪፍና ቀረጥ ምጣኔን ማሻሻል፤ የወጪ ገበያ የምርት አይነቶችን ማስፋትና ሃገራቱን በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር የየሃገራቱን የተናጠል ጥረትና የህብረቱን አመራሮች የጋራ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራቱን በማስተባበር ባለፉት 60 ዓመታት ያለፈበትን የውጣ ውረድ ጉዞ በማጤን የተሻለ ነገን ለመገንባትና የአፍሪካን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከትላንቱ በበለጠ መትጋት ይገባዋል።
"እንሰትና ሁለገብ ጠቀሜታው"
May 6, 2023 1371
በፍሬዘር ጌታቸው እንሰት በኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ያስቆጠረ፤ በተለይ በደቡቡ የሀገሪቱ ክፍሎች በስፋት የሚመረት ተክል እንደሆነ የታሪክ ድርሳናትና በዘርፉ የተካሄዱ ጥናቶች ያስረዳሉ። እንሰት በደቡብ የሀገራችን ክፍል በሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝብች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ነውና የምግብ ዋስትና አለኝታ ተደርጎ የሚወሰድ ተክል ነው። ተፍቆ ለምግብነት ወሳኝ የጤንነት መጠበቂያና የጥንካሬ መሰረት ተደርጎ ይወሰዳል። የእንሰት ተክል የሚጣል ነገር የለውም። ተረፈ ምርቱ ለእንሰሳት መኖ ጭምር ያለው ፋይዳ የላቀ ነው። እያንዳንዱ የእንሰት ተክል ክፍል ከምግብነት ባሻገር ለተለያዩ አገልግሎቶች ይውላል። የእንሰት ተክል ለም አፈር በንፋስና በጎርፍ ታጥቦ እንዳይወሰድ የመከላከል አቅሙ ከፍተኛ ነው። ከዚህም ባሻገር የአፈር ለምነትን እና እርጥበት ጠብቆ በማቆየት ለምርታማነት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ ከደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች ሕዝቦች ጋር ያለውን ቁርኝት ዘመን ተሻጋሪ ያደርገዋል። ለአብነትም እንሰት በወላይታ ብሄር ከሰውና ከእንስሳት ምግብነት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን በአካባቢው "ኡታ" ተብሎ ይጠራል። እንሰት ወይም "ኡታ" የባለፀጋነት መገለጫም ነው። የመኖሪያ ቤቱን ዙሪያ፣ ቀዬውን በእንሰት የከለለና ያስዋበ፣ ማሳውን በእንሰት ያለማ አባወራ ባለጠጋ እንደሆነ ይታመናል። አባወራውም "አላ ኡታ ጎዳው" በማለት ይሞካሻል። እንሰት ለምግብነት፣ ለመደኃኒትነት፣ ለአካባቢ ውበት፣ ለአፈር እርጥበትና ለምነት ለመጠበቅ፣ ለእንሰሳት መኖነት፣ ለባህላዊ ቤት ስራ ጣራና ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት ያገለግላል። እንዲሁም ኮባው (ቅጠሉ) እንደ ዳቦ ለመሳሰሉት ምግብ ማብሰያና ለተለያዩ የግብርና ዉጤቶች መጠቅለያነት ግልጋሎት ይውላል። ከእንሰት ተረፈ ምርቶች የመቀመጫና የወለል ምንጣፎችን ጨምሮ በርካታ መገልገያዎች ይሰራሉ። የእንሰት ተክል በተለያዩ አካባቢያዊ ሁኔታ መብቀል ከመቻሉ ባሻገር ድርቅን የመቋቋም አቅሙ ከፍተኛ ነው። በዚህም አካባቢው ላይ ድርቅ በተከሰትበት ወቅት "ነፍስ አድን" የሚል ስያሜም ተሰጥቶት እንደነበር በታሪክ ይናገራል። የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር መለሰ መኮንን እንሰት ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥና የልማት ችግሮችን ከማቃለል አንጻር ከፍተኛ ሚና ያለው ነው ይላሉ። ተክሉ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብና በሲዳማ ክልሎች በስፋት እንደሚለማና በሀገሪቱ ከ3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በላይ በተለያየ የእንሰት ዝርያ መሸፈኑን ያስረዳሉ። ከሀገሪቱ ህዝቦች ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የእንሰት ተዋፅኦን የሚመገቡና የሚገለገሉ ናቸው። የእንሰት ተክል በባህሪው የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም የከፍተኛ አቅም ያለው በመሆኑ፤ ለዝናብ እጥረትና ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ተክሉን በስፋት በማልማት የምግብና ዋስትናን በዘላቂነት ማረጋገጥ ይቻላል ይላሉ። እንሰትን ለምግብነት ከመጠቀም ባሻገር ለገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ ሀብት በመሆኑ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የተሻለ አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ጥረት ማድረግ ይጠይቃል ሲሉ ያስረዳሉ ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር መለሰ። እንሰት በአካባቢው ማስገኘት ከሚገባው ጠቀሜታ አንፃር ሲታይ እየሰጠ ያለው ጥቅም ከአቅም በታች ነው የሚሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የእንሰት ሰብል ተመራማሪ ዶክተር አብርሃም ቦሻ ናቸው። በመሆኑም የእንሰትን ምርታማነት ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲው የምርምር፤ የማህበረሰብ አገልግሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን በትኩረት እየሰራ ነው ይላሉ። በኢትዮጵያ ከባህር ጠለል በላይ ከ1 ሺህ 500 እስከ 3 ሺህ 100 ሜትር ከፍታና አማካይ የዓመት ዝናብ መጠን ያለው አካባቢ ለእንሰት ተክል ምቹ ሲሆን፤ እንሰት ዝናብን የሚተካ አማራጭ የውሃ ምንጮች ባሉበት አካባቢ ከ1 ሺህ 500 ሜትር በታች በሆኑ ቆላማ አካባቢዎችም ምርት ሊያስገኝ ይችላል ይላሉ። እንደ ተመራማሪው ገለጻ እንሰት በሀገሪቱ ከሚገኙና ዋና ዋና ሰብሎች ከሚባሉት መካከል አንዱና ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው ነው። ተክሉ ተራራማ ቦታዎች ላይ ጭምር በምቾት የሚያድግ ሲሆን እንደ ዝርያው ዓይነት ከሶስት እስከ አምስት ዓመት ውስጥ ምርቱ ውጤታማ መሆን ይችላል። ዝርያው "ወንዴ" እና "ሴቴ" ተብሎ የሚከፈል ሲሆን፤ 60 ያህል የእንሰት ዝርያዎች አሉ። ከምርት አያያዝና ብቃት አንጻር ሲታይ ከእያንዳንዱ የእንሰት ተክል ከ40 ኪሎ በላይ ዱቄት ይገኝበታል። እንሰት ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ጉልህ አስተዋፅኦ ያለው ሰብል ነው፤ ከዛም አልፎ ለሰውና ለእንስሳት ከተለያየ በሽታ የመከላከልና ከጉዳት ለማገገም የሚያስችል መድኃኒት ነው። ተክሉን የማባዛት ስራ በባህላዊ መንገድ የሚከወን ሲሆን፤ የእንስሳትና ሌሎች የሚወገዱ ተረፈ ምርቶችን በመጨመር እድገቱን ውጤታማ ማድረግ ይቻላል። ከእንሰት ምርት የሚገኘው ዱቄት ቡላ ወይም በአካባቢው አጠራር "ኢቲማ" ለልጆችና ለአዋቂዎች ጤና ተስማሚ ሲሆን፣ ገንፎ፤ የክትፎ የአይብና ጎመን ማባያ ቆጮ "ኡንጫ" እንዲሁም ሙቾና ባጭራ ለምግብነት ከሚውሉት ተጠቃሽ ናቸው። የእንሰት ተክል በተለያዩ የአፈር ዓይነቶች ላይ የሚለማ፣ የአየር ንብረት ለውጡን የመቋቋም አቅም ያለው ተክል ነው። የወላይታ ዞን እንሰት አብቃይ ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ ሲሆን በተለይም በባይራ ኮይሻ፣ በቦሎሶ ሶሬና በአንዳንድ የሶዶ ዙሪያ ወረዳዎች በተደረገ የዳሰሳ ጥናት የእንሰት ተክል የመመናመንና የበሽታ አደጋ እንደተጋረጠበት ዶክተር አብርሃም አብራርተዋል። ለዚህም ምርቱን መልሶ ለማስፋፋትና ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ከዞኑ ግብርና መምሪያ ጋር በመሆን በትብብር እየተሰራ መሆኑን ያስረዳሉ። የወላይታ ዞን የግብርና መምሪያ እርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዓለሙ እንዳሉት በወላይታ ዞን ከ28 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በእንሰት ተክል የተሸፈነ ነው። የእንሰት ተክል የሚፈለገውን ምርትና ውጤት እንዳይሰጥ ከሚያደርጉ ተግዳሮቶች መካከል ዋነኞቹ የአጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ፣ የተለያዩ ተባዮች፣ ፍልፈልና ጃርት ይጠቀሳሉ። የእንሰት አጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ በሁሉም የእንሰት አብቃይ ስነ-ምህዳር የሚገኝ፣ በሁሉም የእድገት ደረጃ ላይ ያለን የእንሰት የሚያጠቃና ከአንዱ ወደ ሌላው ተክል የሚተላለፍ መሆኑ ችግሩን የከፋ ያደርገዋል። በመሆኑም ችግሩን ለማስወገድ ጤነኛ የእንሰት ተክሎችን በላቦራቶሪ የማባዛት፣ የበሽታ አምጪ ተህዋሲያን የማጥናትና በጄኔትክ ምህንድስና በሽታን የሚቋቋም ቅንጣት ወደ እንሰት የማስገባት ሥራ እየተሰራ ነው። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ከሶዶ ግብርና ኮሌጅ እንዲሁም ከአረካ የምርምር ማዕከል ጋር በመሆን በጋራ እየተሰራ ነው። ኃላፊው እንዳስረዱት ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በሽታን የሚቋቋሙ ከ20 ሚሊዮን በላይ የእንሰት ችግኞችን አባዝቶ በመትከል የተሻለ ውጤት እየታየ ነው። ይህን ሥራ በማጠናከር ከእንሰት ዘርፍ ሊገኝ የሚገባውን ጥቅም ለማግኘት አርሶ አደሩ ያለውን አገር በቀል ዕውቀቱን በአግባቡ እንዲጠቀም በከፍተኛ ንቅናቄ እየተሰራ ይገኛል። በዚህም የአካባቢውን የእንሰት ሽፋን ማሳደግ ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሩን ጥያቄ መመለስና ጥቅሙን ለማላቅ የተጀመረው የንቅናቄ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ወሳኙ ስራ ተደርጎ እየተከናወነ ነው። ማህበረሰቡ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የአየር ንብረት ፋይናንስ-አፍሪካውያን ገፍተው ያልሄዱበት መንገድ
Feb 18, 2023 1700
/በገዛኸኝ ደገፉ/ የአፍሪካ ቀንድ ከ40 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ አያቅም የተባለለትን የድርቅ አደጋ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ሆነዋል። የድርቁ አደጋ የከፋበት የአፍሪካ ቀንድ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ተሸክመዋል። በተጨማሪም የከተሞች መስፋፋትና የከተሜነት የኑሮ ዘይቤን እያስተናገደች ባለችው አፍሪካ የኃይል እጥረት፣ በቂ የመሰረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ አለመኖር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት፣ ሥራ አጥነት ብሎም የወንጀሎች መስፋፋት አሕጉሪቱን ክፉኛ እየፈተኗት ይገኛሉ። የገጠር መሬት ምርታማነት መቀነስ ከገጠር ወደ ከተማ ለሚደረገው ፍልሰት አንደኛው ገፊ ምክንያት ሲሆን ለመሬቱ ምርታማነት መቀነስ ሰበብ ተደርጎ በዋናነት የሚጠቀሰው ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት የሚወልዳቸው የውኃ ኃብት መቀነስና ለተከታታይ ዓመታት የሚዘልቁት የድርቅ አደጋዎች መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አወሳስቦታል። እንደ አህጉር ከ4 በመቶ ያነሰ የካርቦን ልቀት ያላት አፍሪካ 65 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ መሆን ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚህ ችግር ሙሉ ለሙሉ መውጣት ባይቻልም ትርጉም ባለው ደረጃ መቀነስ እንዲቻል አህጉሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ኃብትና ወጣት የሰው ኃይል በማስተሳሰር ለውጥ ማምጣት ግድ ይላታል። በአፍሪካ የማይቀረውን የከተሞች መስፋፋትም ሆነ የህዝቦቿን የመልማትና የመለውጥ ፍላጎት ማሟላት ካለባት የአየር ንብረት ፋይናንስን የበለፀጉ ሀገራት ገቢራዊ ሊያደርጉት ይገባል። የአየር ንብረት ፋይናንስ (Climate Finance) የአካባቢ፣ ብሔራዊ ወይም ድንበር ተሻጋሪ ፋይናንስን የሚመለከት ሲሆን ከሕዝብ፣ ከግል እና ከአማራጭ የገንዘብ ምንጮች የተውጣጣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ስምምነት ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል እና የፓሪስ ስምምነት ደግሞ ሰፊ የገንዘብ አቅም ካላቸው አገራት አነስተኛ የኃብት አቅም ላላቸው እና ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ አገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት ነው። ስምምነቱ “የጋራ ግን ደግሞ ልዩነት ያለው ኃላፊነትና አቅም” በሚለው መርህ መሰረት ያደጉ አገሮች አዳጊ አገራትን ለመርዳት የገንዘብ ምንጮችን እንዲያቀርቡ ይጠይቃል። ፋይናንሱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ወሳኝ ድጋፍ እንደሚሆን ታምኖበታል። ምክንያቱም ልቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ላቅ ያለ የኢንቨስትመንት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ። በተመሳሳይ ከአሉታዊ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎች ጋር ለመላመድ እና ተለዋዋጭ ጫናዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። ከጥቂት አሥርት ዓመታት በፊት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የምእተ ዓመቱ የልማት ግብ ሰነድም ሆነ በቅርቡ በሚጠናቀቀው ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት ቢሰጠውም እስካሁን ግን የፈየደው ነገር የለም። አፍሪካ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችን ለመላመድ ዓመታዊ 41 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ክፍተት ይገጥማታል። ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ እያስተናገደች ባለችው 36ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ የአየር ንብረት ፋይናንስ ገቢራዊ ማድረግን ቀዳሚ ትኩረታቸው መሆን እንዳለበት የአንድ ዘመቻ (ONE Campaign) አጽንኦት ሰጥቶ ምክረ ሃሳቡን ሰንዝሯል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የአንድ ዘመቻ ዳይሬክተር ዶሪን ኒኒናሃዝዌ የአፍሪካ መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመላመድ ፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን አስከፊ ተጽዕኖ የመቋቋም አቅም እንዲገነቡ መክረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝቦቿ ለከፋ ጥቃት እየተዳረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች የበለጸጉ አገሮች የገቡትን የማላመድ ፋይናንስ ድጋፍ ቃል እንዲፈጽሙ ከማግባባት ባለፈ ማሳሰብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ ማለት እኤአ ከ2020 እስከ 2025 በዓመት 100 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመተውን ግብ የማሳካት ተግባር የሚጠይቅ ነው። ከዚህ ባሻገር በቀጣዮቹ ዓመታት በተጨመሩ መዋጮዎች የሚስተዋሉ ጉድለቶችን መፍታት እና በግብጿ ሻርም ኤል ሼክ ከተማ ባስተናገደችው COP-27 ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ለመላመድ በእጥፍ ፋይናንስን የማቅረብ ቁርጠኝነት የማቅረቢያ ዕቅድ ሊነድፉ ይገባል ነው ያሉት። የአፍሪካ አገሮች ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ጋር ሲታገሉ ቢቆዩም አሁን ላይ “አፍሪካ በአፈፃጸሙ ላይ መጠነኛ መሻሻል አሳይታለች” ብለዋል። እናም በ36ኛው የመሪዎቹ ጉባዔ የተገኙ ስኬቶች እና የጠፉ ዕድሎች እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማዎች ለማሳካት በአየር ንብረት ፋይናንስ በጥልቀት መክረው ለተሻለ ስኬት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዋና ዳይሬክተር አንቶኒዮ ቪቶሪኖ በአየር ንብረት ምክንያት የሚፈጠሩ መፈናቀልን ለመግታት የተሻሻሉ የመላመድ እና የተጽዕኖ ቅነሳ ተነሳሽነት ገቢራዊ ለማድረግ በአገራት መካከል ጠንካራ አጋርነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያሰምሩበታል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ኑሯቸውን መሰረት ባደረጉ ህዝቦች ላይ አውደ-ተኮር መላመድ እና የመቋቋም አቅም ግንባታ መፍጠር ይገባል። ለዚህ ደግሞ መላመድን የሚደግፉ ፋይናንስ ለማግኘት የሚረዱ መመሪያዎች ይበልጥ የተፍታቱ መሆን ይኖርባቸዋል ሲሉ ቪቶሪኖ ይሞግታሉ። ከ 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተጓዳኝ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ (High-Level Forum) ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በሻርም ኤል ሼክ በተካሄደው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መላመድን፣ መከላከልን እና ዝግጁነትን ለማሻሻል ዓለም አቀፍ ትብብር ማጎልበት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አውስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ ያወጣቸው የስምምነት ማዕቀፎች (United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC)) በርካታ ዝርዝርና ሚዛናዊ አካሄዶችን የያዙ ናቸው። ያም ሆኖ አተገባበራቸው እዚህ ግባ የማይባል በመሆኑ የሚታሰበውን ያህል ለውጥ ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። በዚህም ቦረና ዞንን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የአየር ንብረት መዛባት፣ የሙቀትና የባህር ጠለል መጨመር፣ ጎርፍ፣ ድርቅ እንዲሁም ያልተገመቱ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። ዳሩ ግን አገራትን፣ አህጉርን፣ ዓለምን እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ግዙፍ ኩባንያዎችን ያስተሳስራል የተባለለት የአየር ንብረት ፋይናንስ በቅጡ ገቢራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች ዳፋውን ለመጋፈጥ ተገደዋል። የአየር ንብረት ፋይናንስን በመተግበር በመስኩ የተጎጂዎችን ቁጥር ሊቀንሱና የዓለምን ሥነ-ምህዳር ከተቻለ ወደ ቀድሞው ሊመልሱ አሊያም አሁን ባለበት አረጋግተው ሊያቆዩ የሚያስችሉ በርካታ አማራጮች ተግባራዊ ሊደረጉ ይገባል። ለአብነትም ለድሃ ሃገራት አርሶ አደሮች የግብርና ምርቶች ተገቢውን ዋጋ በመክፈል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን እንዲቋቋሙ ማድረግ ከአማራጮቹ መካከል አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግዙፎቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሚያስወግዷቸው በካይ ጋዞች ተመጣጣኝ የጤና ሥርዓት በመዘርጋት የታዳጊ ሃገራት ዜጎችን የጤና አገልግሎት ማሻሻል ሌላው አማራጭ ነው። የተፈጥሮ ኃብቶችን የሚጎዱ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተፈጥሮን በሚንከባከቡ ዘዴዎች መተካት እንዲሁም ብክለትን የሚያስቀሩ የምርት ሂደቶች መለማመድ ጥቂቶቹ የመፍትሄ አማራጮች ተደረገው የሚወሰዱ ናቸው። በፓሪስ ከተደረሰውን የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ 1994 ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም (Global Environment Facility-GEF) COP-16 ዓለም አቀፍ ጉባዔ በኋላ በ2010 አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund-GCF) እንዲሁም በ2001 ደግሞ ልዩ የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (Special Climate Change Fund-SCCF) እና የመላመድ ፈንድ (Adaptation Fund-AF) የተባሉ ማዕቀፎች የተዘጋጁ ቢሆንም ስለጉዳዩ የሚያስረዱ ተከታታይ ስብሰባዎች ከማዘጋጀት በዘለለ ብዙ ርቀት መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። በቅርቡ በአለም ባንክ አሰባሳቢነት በኬንያ ናይሮቢ ተዘጋጅቶ በነበረው የአህጉሪቱን መሪዎች ባለሃብቶችንና ምሁራንን ባካተተውና “One Planet Summit” በተሰኘ መሰል ጉባዔ ላይም አፍሪካውያን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚገጥማቸውን ችግሮች ተከላክለው ሁለንተናዊ ዕድገታቸውን እንዲያፋጥኑ ካስፈለገ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምጣኔ ኃብት ፖሊሲ አዘጋጅተው መተግበር እንደሚኖርባቸው መግባባት ላይ የተደረሰ ቢሆንም አሁንም ጥያቄ ያስነሳው አፈጻጸሙ ስለመሆኑ ብዙ ተብሎለታል። ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ የተባለ ድርጅት ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው አፍሪካ እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር ከ 2020 እስከ 2030 ባሉት አሥር ዓመታት 2 ነጥብ 8 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር አሊያም በየዓመቱ ከ2 መቶ ሃምሳ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን አህጉሪቱ ከዘርፉ እያገኘችው ያለው ገንዘብም ከሚያስፈልጋት 12 በመቶውን ወይም 30 ቢሊየን ዶላር ብቻ ስለመሆኑ አስነብቧል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ሊሰሩ የሚችሉ በርካታ ተግባራት እንዳሏት የሚያትተው ሪፖርቱ ከአየር ንብረት ፋይናንስ የሚገኘው ገንዘብ በትራንስፖርት፣ በኃይል ልማት፣ በኢንዱስትሪ ብሎም በግብርና፣ በአፈርና በደን ኃብት አጠቃቀም ውጤታማ በሆነ መንገድ ከዋለ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ኃብቶች መንከባከብ ከማስቻሉም ባለፈ ላቅ ያለ ፋይዳ ይኖራዋል ብሏል። ይህ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖው ያስረዳል። ላለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ገቢራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራን የማስፋፋትና የተጎዱ አካባቢዎችን የማከም ሥራ እንዲሁም አይቀሬ የሆኑትን ከተሜነትና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ታሳቢ ያደረጉ የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ለአፍሪካ ሃገራት እየፈጠረው ያለው በጎ ተጽዕኖ በግልጽ እየታየ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ጥረት ግን በአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲደገፍ አገራዊና የተቀናጀ አሕጉራዊ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል። ከአጠቃላይ የአፍሪካ አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ግብጽ ብቻ 151 ቢሊየን ዶላር ከአየር ንብረት ንብረት ፋይናንስ ማግኘት እንደሚኖርባቸው የክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ ሪፖርቱ ይገልጻል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በመጭው የCOP-28 ጉባዔ የራሷንና የአፍሪካን ፍላጎት የሚያስጠብቁ የፋይናንስ ትልሞችን የመንደፍ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ የ COP-27 ጉባዔ ለአፍሪካ ያስገኘውን ውጤት እና አንድምታ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የመሪዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አስተባባሪ በሆኑት በኬንያው ፕሬዝዳንት ሰብሳቢነት በኅብረቱ የአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ በጥልቀት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ጥረቷን የሚያጎለብት የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ጠንካራ ተሳትፎ ልታደርግ ይገባል። የአፍሪካ አገራት ገፍተው ረጅም ርቀት ያልሄዱበት የአየር ንብረት ፋይናንስ እና ሌሎች የድጋፍ አማራጮችን በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት በመጠቀም የአየር ንብረት ተጽዕኖን የሚቋቋሙበት ጠንካራ አቅም ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል። በእርግጥም አፍሪካውያን መሪዎች በሚያደርጉዋቸው ስብሰባዎች በየማዕዝናቱ በድርቅ ሳቢያ ለምግብ እጦት የተዳረጉ ህዝቦቻቸውን የሚታደጉበት ሁነኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበትን ዘዴ ነድፈው ረጅም ርቀት ሊጓዙ ይገባል። ”
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 2090
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 4886
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት። እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 1970
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል። “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 2161
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
መጣጥፍ
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 3293
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ)
Jan 25, 2023 2776
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ) አየለ ያረጋል (ኢዜአ) መዳረሻዬ ሽሬ እንዳስላሴ ነው። ለዘገባ ሥራ ከባህርዳር- ጎንደር- ደባርቅ- ሸሬ መንገድ ከሚዲያ ባልደረቦች ጋር እየተጓዝኩ ነው። የጥምቀት ሙሽራዋ ጎንደር እየተኳኳለች ነበር። ደባርቅ ከመድረሴ በፊት ዳባት ትገኛለች-የደጃች አያሌው ብሩ ቁርቁር ከተማ። ደጃች አያሌው ትውልዳቸው በጌምድር ጋይንት ቢሆንም ግዛታቸውና ኑሯቸው ዳባት ነበር። ሞገደኛው ደጃዝማች አያሌው ብሩ በጎንደር ማኅበረሰብ ዘንድ ዝናቸው የናኘ ነው። ደጃዝማች አያሌው በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ (ከልጅ ኢያሱ እስከ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ-መንግሥት) ታሪካዊ ክንውኖች ጉልህ ተሳትፎ አላቸው። አንዷን ብቻ ልምዘዝ። ራስ ተፈሪ ‘ንጉሠ-ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ’ ደጃች አያሌው የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ ጉግሳ ወሌ ብጡልን (የንግሥት ዘውዲቱን ባለቤት) ወግተው የጎንደር ግዛት ‘ራስ’ ተብለው ለመሾም ቃል ቢገባላቸውም፤ ተልዕኳቸውን ተወጥተው ቃሉ ባለመፈጸሙ ደጃዝማቹ ከአጼው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። በዚህም:- "አያሌው ሞኙ፣ ሰው አማኙ ሰው አማኙ፣ የአያል ጠመንጃ፣ ስሟን እንጃ ስሟን እንጃ…” በማለት የጎንደር አዝማሪ አዚሟል። ዛሬም ይህ ግጥም የብዙ ባህላዊ ዘፈኖች አዝማች ነው። ደጃች አያሌው ብሩ ደፋር ናቸው ይባላል። ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር ቢቀያየሙም በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ሲመጣ ቅድሚያ ለአገሬ ብለዋል። ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘው የዶክተር ሀራልድ ናይስተሮም (ትርጉም ገበየሁ ተፈሪ እና ደሳለኝ አለሙ) መጽሐፍ እንደተጠቀሰው ደጃች አያሌው “ንጉሡ እንደኛ ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሁላችንም ናት" ብለው ጦራቸውን መርተው በሽሬ ግንባር ዘምተዋል። ጉዟችን ቀጥሏል። ደባትን እያለፍን ነው። ‘እንኳን ደህና መጡ፤ ወደ ጭና ታሪካዊቷ ሥፍራ’ የምትለዋን ታፔላን በስተግራ እያየን ወደ ደባርቅ ገሰገስን። የሰሜን ተራሮች የብርድ ወጨፎ ያረሰረሳትን ደባርቅን ከማለፋችን ሊማሊሞ ጠመዝማዛ ቁልቁለት ተቀበለን። አስፈሪ የሊማሊሞ መልክዓ ምድር የደጋው ሰሜን ውርጭ እና የተከዜ በርሃ ኬላ ነው። ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህን “የሰማይ የምድሩ ኬላ፣ የየብስ የጠፈሩ ዋልታ አይበገር የዐለት ጣራ፣ አይመክተው መከታ ሊማ-ሊሞ አድማስ ሰበሩ፣ በጎማ ፈለግ ይፈታ? በትሬንታ እግር ይረታ?…” ብሎ የመኪና መንገድ ተገንብቶበት በማየቱ ግርምቱን የተቀኘለትም ለዚህ ይመስላል። ከሊማሊሞ ቁልቁለት በኋላ አዲ-አርቃይ፣ ዛሪማ፣ ማይፀብሪ እና ሌሎች የጠለምት ወረዳ ከተማዎችን አልፈን፤ የዋልድባ ረባዳማ አካባቢዎችን ተሻግረን ተከዜ ወንዝ ደረስን። የዚህን መንገድ እና ተከዜ ወንዝን ሳስብ የሀዲስ ዓለማየሁ ትዝታ አስተከዘኝ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር የወገንን ጦር ፊት ለፊት መቋቋም ሲሳነው በሰው ልጆች ላይ ተደርጎ የማያውቅ መርዝ በጅምላ የፈጀበት አሳዛኝ ታሪክ ነበር። በተከዜ ወንዝ ውሃን በመመረዝ የወገን ጦር ያለቀበት ሥፍራ ነው። የተከዜ ሸለቆ በኢትዮጵያዊያን ደምና አጥንት ዋጋ የተከፈለበት ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በአንድ ዕለት የተመለከቱትን እንዲህ ጽፈውታል። “የተከዜ ውሀ እመሻገሪያው ላይ ሰፊና ፀጥ ያለ ነው። ታዲያ ያ ሰፊ ውሀ፤ ገና ከሩቅ ሲያዩት ቀይ ቀለም በከባዱ የተበጠበጠ ይመስላል። “ምን ነገር ነው፤ ምን ጉድ ነው?” እየተባባልን ቀረብ ስንል መሻገሪያው በቁሙም በወርዱም ከዳር እስከ ዳር ሬሳ ሞልቶበት የዚያ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው። የሰው ሬሳ፣ የፈረስ እና የበቅሎ ሬሳ፣ ያህያ ሬሳ፣ ያውሬ ሬሳ፥ ሬሳ ብቻ! እግር ከራስ ራስ ከእግር እየተመሰቃቀለ እየተደራረበ ሞልቶበት፥ የዚያ ሁሉ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው”። ይሉናል። ቀጥለውም “በእውነቱ እንዲህ ያለውን መሳሪያ ምንም ጠላት ቢሆን በሰው ላይ ለማዋል የሚጨክን ሰው፥ ሰብዓዊ ስሜት የሌለው፣ አለት ድንጋይ የተፈጠረበት መሆን አለበት፤ እንዲህ ያለውን መሳሪያ በሰው ላይ ማዋል ሰብዓዊ ህሊና ሊሸከመው የማይችል እጅግ ከባድ መሆኑን ዓለም ሁሉ ያወቀውና ያወገዘው በመሆኑ የኢጣሊያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ከማድረጉ በቀር “ሌላ መንግሥት በሌላ አገር ላይ አደረገ’ ሲባል ተሰምቶ የሚያውቅ አይመስለኝም” ብለዋል። ከተከዜ ባህር ማዶ ጉዞዬ ያገኘኋት ሌላዋ ታሪካዊ ሥፍራ እንዳባጉና ናት። እንዳባጉና የወገን ጦር ትልቅ ገድል የፈጸመበት ነው። ጀግኖች አባቶቻችን የጠላት ታንክ ሳያስፈራቸው የጠላት ጅምላ ጨራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ተቋቁመው ጠላትን ድባቅ የመቱበት፤ ወደ አክሱም እንዲያፈገፍግ ያደረጉበት ሥፍራ ነው። “የጠላት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በጦር ሜዳው ትንንሽ ቦምቦች አውቶማቲክ ጠመንጃ ይተኩስ ነበር። አቢሲኒያኖች ደግሞ ከጠላት ጋር ግብግብ ገጥመው ጉዳይም አልሰጡትም ነበር…” ይላል ዶክተር ሀራልድ ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘ መጽሐፉ። ይህ አካባቢ በሀገር ፍቅር የነደዱ ኢትዮጵያዊያን ደም ያፈሰሱበት፣ አጥንት የከሰከሱበት፤ ለኢትዮጵያ መስዕዋትነት የከፈሉበት ነው። ይህ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ቀጣና ነው። ቀኑ ተገባዷል። ጉዟችን እንደቀጠለ ነው። እኔም የማሽላ ማሳዎችን ግራ ቀኝ እየተመለከትኩ ለዕለቱ መዳረሻችን ወደሆነችው ሽሬ ከተማ ገባን። ሽሬ በትግርኛ ‘ሽረ’ ሲሉት ይደመጣሉ። በእርግጥ ሽሬን ለመጀመሪያ ጊዜ መርገጤ ነው። ዕለቱም ጥር ሥላሴ ነው። ሽሬ በጥር ሥላሴ ትደምቃለች፤ ሙሉ ስሟም ሽረ እንዳስላሴ ነው። የሽሬ ሥላሴ ጠበል ሽሬ ደርሰን ማረፊያችንን ያዝን። ጊዜው በጣም አልመሸምና ከተማዋን በቀላሉ መቃኘት ይቻላል። ሽሬ ሰፊና ደማቅ የዞን ከተማ ናት። ከመካከላችን የአንደኛው ባለሙያ ቤተሰቦች ሽሬ ነበሩና አስጠሩን። ለሥላሴ ጠበል ግብዣ። ባል እና ሚስቱ ከልክ በላይ መስተንግዶ አደረጉልን። ‘ጠብ እርግፍ አድርገው አስተናገዱን’ ማለት ይቀላል። እንግዳ መቀበል ነባር ኢትዮጵያዊ እሴታችን ቢሆንም ጦርነት ውስጥ ለቆየ አካባቢ የተለየ መልክ ነበረው። እንግዳ አቀባበላቸው በእርግጥም የመሃል አገር ሰው የናፈቃቸው ይመስላል። የተትረፈረፈ እህልና ውሃ አቅርበው በ’ብሉልን፤ ጠጡልን’ ተማጽኗቸው የተነፋፈቀ ቤተ-ዘመድ ግብዣ አስመሰሉት። የሥላሴው ጠበል የሸሬ ጠላ ቀረበ። የሸሬ ጠላ ሳስታውስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ታወሱኝ። የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምሀሩ ፕሮፌሰር ሽብሩ በዘመነ ደርግ በዕድገት በሕብረት ዘመቻ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ሽሬ ዘምተው ነበር። በወቅቱ ታዲያ የሸሬ ጠላ ፍቅር ይዟቸው በየጊዜው ሲኮመኩሙ የተመለከቱ ሰዎች ‘ፕሮፌሰሩ ከጠፉ የሚገኙት ጠላ ቤት ነው’ ሲባሉ እንደነበር ‘ከጉሬ ማርያም እስከ አዲስ አበባ’ በተሰኘው ግለ ታሪካቸው አስፍረዋል። ከግብዣ መልስ ከማረፊያ ሆቴል ላይ ሆኜ ከተማዋን ስቃኛት ከጦርነት ድባቴ የተላቀቀች ይመስላል። የአመሻሽ ሕዝቡ እንቅስቃሴም ሆነ እስከ ሌሊቱ አጋማሽ የሚሰሙ የመዝናኛ ቤቶች ሙዚቃዎች የከተማዋን አሁናዊ መልክ የገለጠልኝ ነበር። ንጋት ላይ በቁርስና ቡና ሰዓታት ከሰዎች ጋር መስተጋብሬ ጀመረ። በጦርነት አዙሪት የከረመችው ሽሬና አካባቢው ኑሮ እጅጉን የከበደ ነበር። መልከ-ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች አስተናግደዋል። አሁናዊ ምላሻቸው “ተመስገን፤ ያ ሁሉ አለፈ” የሚል ነው። ገበያው ተረጋግቷል፤ ማህበራዊ ኑሮ ተመልሷል። ድህረ-ሰላም ስምምነት ለሽሬ ነዋሪዎች ሁለንተናዊ እፎይታን አንብሯል። ከቀናት በኋላ በአክሱም የታዘብኩትም እንዲህ ነው። ኑሮን ያቀለለው የተቋማት አገልግሎት ጅማሮ በመጀመሪያ ዘገባ ስራዬ መሰረተ ልማትን አገልግሎት ቃኘሁ። ባንክ፣ ቴሌ፣ ሆስፒታል… መሰሎቹን። ተጠቃሚዎችንም፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ስራ ሃላፊዎችንም አነጋገርሁ። ከሰላም ስምምነቱ ማግስት ጀመሮ ተቋማቱ ወደስራ መመለሳቸው ከሁለንተናዊ ችግር እንደታደጋቸው ያነሳሉ። በትራንስፖርት እየተንቀሳቀሱ፣ በኤሌክተሪክ ስራዎቻቸውን እየከወኑ ነው። ለሁለት ዓመታት የተቋረጠው አገልግሎት አቅርቦት እና የአገልግሎት ፈላጊዎች ፍላጎት ግን አሁንም ሙሉ በሙሉ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ የተጠቃሚዎችም፤ የአገልግሎት ሰጭዎችም ሀሳብ ነው። በሽሬ ስሁል ሆስፒታል የተመለከትኳቸው፤ ያነጋገርኳቸው፤ ከታዳጊዎች እስከ አዛውንት ዕድሜ ያሉ ህሙማን የሰላም አየር ማግኘታቸው የሕይወታቸው ዑደት እንዲቀጥል አድርጓል። ድንገተኛም ሆነ ነባር ህመም ያለባቸው ሰዎች በነጻ እየታከሙ ነው ያገኘኋቸው። ሰላም ከሌለ መታከም ቀርቶ በቅጡ ማስታመም፤ በወጉ መቀበርም እንደማይቻል ገልጸውልናል። የጤና፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት የግብዓት ክፍተቶች የማሟላት ሰራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም በፌዴራል ደረጃ በየተቋማቱ የተመደቡ አስተባባሪዎች አረጋግጠውልኛል። የጸጥታ አካሉና የህብረተሰቡ ትብብርም የሚያስቀና እንደሆነ ግለሰቦችም፤ የጸጥታ አካላትም ነግረውኛል። አክሱም ጺዮን ማርያም፣ ሽሬ ስላሴ ንግስ፣ የጥምቀት በዓላት ከሶስት ዓመታት በኋላ በአደባባይ ታቦት ወጥቶ ተከብሯል። የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮችም ይህንኑ ነው ያረጋገጡልኝ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት ቤተሰባዊ የሆኑ ይመስላል። እንቅስቃሴያቸውም የሰላማዊ ቀጠና መልክ ያለው ነው፤ ዩኒፎርም ከመልበሳቸው በስተቀር ጀሌያቸውን ይንቀሳቀሳሉ። ይህ ደግሞ መተማመን ከመፍጠር ባለፈ ጦርነት ውስጥ ለቆየ ማህበረሰብ ከስነ ልቦና ጫና እንዲላቀቅ አይነተኛ ሚና እንደላው ይሰማኛል። ኢ-መደበኛ የሽሬና አክሱም ወጎች ያረፍኩበት ሆቴል ባለቤት ‘አደይ’ ተግባቢ ናቸው። ደግ እናት ይመስላሉ። ከገባን ጀምሮ ‘ጠላ ተጎንጩ፤ ቡና ጠጡ’ ጭንቃቸው ነው። ሁለት ቀን ቡና አስፈልተውልናል፤ ጠላ አቅርበው ዘክረውናል። ይህ ሁሉ ሲሆንም ለከተማው እንግዳ መሆናችንን እንጂ ስለሙያችንም ሆነ ስለሌላ ማንነታችን አያውቁም ነበር። ብዙ መጨዋወትና ውሎ አዳር በኋላ ነው ጋዜጠኛ ስለመሆናችን ያወቁት። አደይ ተጨዋች ናቸው። አማርኛ ያዝ ቢያደርጋቸውም ጨዋታቸው ‘ኩርሽም’ ነው- ተሰምቶ የማይሰለች። በአጋጣሚ ‘ሰለክላካ’ ስለምትባለዋ ታሪካዊ ሥፍራ ጠይቄያቸው እያወጋን ነበር። ‘እንደእናንተ ወጣቶች ሳለን ‘ሰለክላካን ያላዬ ሸዋን ያመሰግናል’ ይባል ነበር። ታዲያ አንድ የሸዋ ሰው መጣና ሰለክላካን አየና ‘በቃ ይቺ ናት’ ሰለክላካ’ ብሎ ተገረመ” ብለው አሳቁን። (የፍቅር እስከ መቃብር መሪ ገጸ-ባህሪው ‘በዛብህ’ ወደ ዲማ ጊዮርጊስ ሄዶ ‘የዲማ መልኳ እና ዝናዋ’ ተጣርሶበት እንደተገረመበት ቅጽበት መሆኑ ነው)። አደይ የተጀመረው ሰላም ፍጹም ምሉዕ ሆኖ ወደ ቀደመ ኢትዮጵያዊ መልካችን የምንመለስበት ጊዜ እንዲመጣ ይሻሉ። ከጦር-ነት ወደ ሰላም-ነት! ቆንጂዬዋ ፊዮሪ የኮሌጅ ተማሪ ነበረች። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጀምሮ በኋላም በጦርነት ሳቢያ ትምህርቷን ካቆመች ሦስት ዓመታት ሆኗታል። ጦርነቱ ከቆመ በኋላ የጀበና ቡና ጀምራለች። ደንበኞቿ ሰብሰብ ብለን እንቀመጣለን። ፊዮሪ ከስኒ ማቅረቢያዋ ላይ አነስተኛ ጀበናዋን፤ የሚያማምሩ ስኒዎቿን እና መዓዛው ከሚያውድ የዕጣን ማጨሻዋ ጋር ሰድራ ይዛ ትቀርባለች። ከመካከላችን ካለው ጠረጴዛ ላይ ታስቀምጥና እርሷም ወንበር ይዛ ከመካከላችን ትቀመጣለች። ቡናው እስኪሰክን ጨዋታዋን ታስኮመኩመናለች። ቡናው ከሰከነ በኋላ ቡናዋን ቀድታ ለእያንዳንዳችን በእጃችን እያነሳች ትሰጣለች። በሽሬ ቡና የሚቀርበው በዚህ መልክ ነው። ለፊዮሪ እና መሰሎቿ ጦርነቱ ክፉ ጠባሳ መጣሉ፤ ተስፋቸው ላይ መጥፎ አሻራ ማስቀመጡን ታነሳለች። አሁን ግን ብሩህ ተስፋ ሰንቃለች። ስለነገዋም “ሰላሙ ይዝለቅልን፤ ትምህርቴን ለመቀጠል እመኛለሁ” ትላለች። አክሱም ከሽሬ በስተሰሜን 60 ኪሎ ሜትር ይርቃል። ከሽሬ አክሱም ስንንቀሳቀስ ከጥምቀት ዕለት በስተቀር ገበሬው የግብርና ሥራዎቹን እየከወነ ነበር። አርሶ አደሩ ያርሳል፤ መስኖውን ያለማል። የተዘራውን ውሃ ያጠጣል። የበቀለ ቡቃያውን ይኮተኩታል። ከጦርነት ወደ ልማት መዞሩን ዐይኔ ታዝቧል። በጥምቀት ዋዜማ፤ የከተራ በዓል ዕለት ሁለት ጎራማይሌ የረፋድ ትዕይንቶችን ላንሳ። ከአክሱም ከተማ ወደ አድዋ እና ሽሬ መገንጠያ አካባቢ ሰፊ የቀንድ ከብት ገበያ ነበር። እውነተኛ የዓመት በዓል ገበያ መልክ ያለው ትዕይንት ነበር። በተለይም የፍየል ዋጋ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተገበያዩ እንደነበር ሰምቻለሁ። ታሪካዊቷን አክሱም ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ የረገጥኳት/የተሳለምኳት ከአራት ዓመት በፊት በ2011 ዓ.ም ይመስለኛል። ከገበያው ቀጥሎ በታቦተ-ጽዮን መገኛዋ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ደጅ፣ በጥንታዊያኑ የአክሱም ሐውልት መገኛ አደባባይ ነበር። ከጽዮን በስተምዕራብ በአርባቱ እንሰሳ በኩል፤ በቅዱስ ያሬድ ዋርካ… አድርጌ በጽዮን ዋናው በር ደረስኩ። ማራኪ የአክሱም የኮብልስቶን መንገዶች ኦና ናቸው። የወትሮው ግርግር ናፍቋቸዋል። ከጽዮን ቅጥር ግቢ በዋናው በር በስተውጭ አነስተኛ እና ብቸኛ ዋንዛ በኮብልስቶን መሃል ነበረች። ዛሬም ለምልማ አለች። በዚህ አካባቢ ድሮ የነጭ ጎብኚ ጋጋታ፣ የጽዮን ደጅ ጠኚ ምዕመን… የተጨናነቀ ነበር። እንደ ድሮው የፎቶ አንሺ ግርግር፣ የአክሱም መስቀል ቀርጸው የሚሸጡ ወጣቶች ጫጫታ የለም። ይልቁንም እርጥባን የሚሹ አቅመ ደካሞችና ህፃናት ነበሩ። ጦርነት የሥፍራዋን መልክ አጠይሞታል። ያም ሆኖ ከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በኩሉሄ ባይባልም ወደነበረበት እየተመለሰ ነው። የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኰች ሥራ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከአክሱም ሐውልት ወደ ሌላ ሰፈር አቀናሁ። ትርሐስ ገና ታዳጊ ልጅ ነች። ጠይም፤ ስርጉድ፣ ሳቂታና ተረበኛ አይነት ልጅ ነች። እንደ ሽሬዋ ፊዮሪ መንገድ ዳር የጀበና ቡና እየሰራች ነው። ከሩቅ የመጣን እንግዶች መሆናችንን ስታውቅ፤ ደስታዋ ከገጿ ይነበብ ነበር። ያለፉ ጊዜያትን ሰቆቃ አጫወተችን። ስለቀጣይ ዕጣ ፈንታዋ እና ዕቅዷ ስታወራ ትቆይና “የሰው ልጅ ግን በጣም ከሃዲ ነው። ከወራት በፊትኮ ስለቢዝነስ አላስብም ነበር። መቼ እሞታለሁ እንጂ” ብላ ራሷን ትወቅሳለች። ወደ ሰማይ አንጋጣ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች። ጦርነት ተራውንም ሕዝብ ለመልከ-ብዙ ቀውስ ዳርጎት እንደቆየ ታነሳለች። ዛሬ ሁሉ አልፎ ሰላም መውረዱ ለመጨዋወት መብቃቷ ለእርሷ ትልቅ ብሥራት ነው። ይህ ለትርሐስ ብቻ ሳይሆን ለመላው አክሱማዊያን መሆኑ እሙን ነው። አክሱም ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በከተማዋ በሻለቃ አዛዥነት የተሰማራ የፌደራል ፖሊስ አባልም ያጋጠመውን አሳዛኝ ገጠመኞች አጫውቶኛል። ጦርነቱ ቢራዘም ኖሮ በተራው ሕዝብ ላይ ምን ያህል የከፋ ጉዳት ይደርስ እንደነበር በአሳዛኝ ሁኔታ ገልጾልኛል። አክሱሞች ያን ሁሉ አልፈው ሰላም አየር ነፍሶ፣ ከስጋት ቆፈን ተላቀው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሰዋል። የዛሬ ሳምንት ሰርክ(11 ሰዓት) ላይ አክሱም የከተራ በዓል በድምቀት አክብራለች። ታቦተ-ጽዮን ወደ ባህረ- ጥምቀቱ ስትወርድ፤ ወግና ሥርዓቱ ተጠብቆ፣ ሕዝቡ በሀበሻ ነጫጭ አልባሳት፣ ካህናት በልብሰ ተክህኖ ደምቀው … እየተከወነ ነበር። አንዲት እናት ለአማርኛ ተናጋሪ በቀረበ አነጋገር እያለቀሱ ታቦት እየሸኙ ነው። ትኩር ብዬ ሳያቸውም ዕንባቸው ዱብ ዱብ ይላል። “ከዚያ ሁሉ መከራ አልፎ ለዚህ በቃን፤ ተመስገን” እያሉ እልልታውን ያቀልጡታል። በደስታ እያነቡ ነበር። ይህ ስሜት የብዙኃኑ አክሱማዊያን እናቶች እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። አክሱም በኮቪድ እና በኋላም በጦርነቱ ምክንያት ባህረ-ምቀት ታቦት ወጥቶ ሲከበር ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ከወትሮው በተለየ ድምቀትና ውበት በሰላምና በደስታ፤ በአደባባይ እልልታና ሆታ በማክበራቸው ልዩ ስሜት ፈጥሮባቸዋልና! እናም በአክሱም የከተራ ሆነ የበዓለ-ጥምቀት ክብረ-በዓላት በሰላም ስምምነቱ ማግስት በድምቀት ተከውኖ አለፈ። የሃይማኖት አባቶቹም ሆኑ ምዕመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅም የዘንድሮው ክብረ-በዓል ካለፉት ዓመታት ነባራዊ ሁኔታ ጋር እያነጻጸሩ፤ ትልቅ ብሥራትና መልክ እንዳለው ገልጸዋል። ሰላም እንዲጸና፤ ነባር ኢትዮጵያዊ አንድነትና መተባበር እንዲመለስ ጽኑ መሻታቸውን ነግረውናል። በበጎ ቀን የማውቃትን አክሱም፤ ከረዥም ጊዜ በኋላ አሁናዊ መልኳን ታዝቤ፤ የነገ ትዝታ ሰንቄ ተመለስኩ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!