ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የክልሉን ሰላም ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Apr 8, 2026 30
ባህር ዳር፤መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በተሰራው የተቀናጀ የህግ ማስከበር ስራ የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፥ የክልሉን ሰላም ለማዝለቅ የተቀናጀ የፀጥታ ማስከበር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ለዚህም የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሎች ከሌሎች የፀጥታ አባላት ጋር በመተባበር የፀጥታ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ባለፉት ጊዜያት በክልሉ የተከሰተው የሰላም እጦት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና መፍጠሩን አንስተው፤መንግስት ችግሩን በመነጋገር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሰፊ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ታጥቀው ጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭን በመቀበል ወደ ሰላማዊ ኑሮ እየመጡ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የክልሉ ህዝብ ሰላምና ልማት አጥብቆ ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ የሰላምን አማራጭ ባልተከተሉ ቡድኖች ላይ የፀጥታ ሃይሉ ህግና ስርዓት የማስከበር ስራውን ህብረተሰቡን ባሳተፈ አግባብ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አክለዋል። የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሉ መጭው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ስጋት መከናወን እንዲችል ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሆነ አስገንዝበዋል። የትንሳኤ በዓልም በሰላም እንዲከበር የተቀናጀ ስምሪት ተሰጥቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመዋል። በበዓል አከባበሩ ወቅት ህብረተሰቡ ማንኛውንም አጠራጣሪ ሁኔታ ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ ሃይል ጥቆማ በመስጠት የሰላሙ ባለቤት መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።
የሰው ተኮር ስራዎቻችን ማንንም የማይዘነጉና አካታች ናቸው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Apr 8, 2026 41
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦መንግስት እያከናወናቸው ያሉ የሰው ተኮር ስራዎቻችን ማንንም የማይዘነጉና አካታች ናቸው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች መጪውን የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ ለማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ፣ለአካል ጉዳተኞች፣ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው የአገር ባለውለታ አረጋውያንና በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የመንግስት ሰራተኞች በአጠቃላይ ከ233 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መደረጉን አመልክተዋል። ይህ ተግባር በከተማዋ የማዕከል መስሪያ ቤቶች፣ በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች በስፋት እየተከናወነ ያለ በጎ ተግባር ነው ብለዋል። ከንቲባዋ አክለውም፥ በሁሉም በዓላት የሚደረገው የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር፣ ድጋፍ የሚሹ የከተማዋን ነዋሪዎች ምን ጎደለ? ብሎ በመመልከትና በመጠየቅ ክፍተታቸውን ለመሙላት የሚከናወንና ለነዋሪዎች ያለውን ክብር የሚገልጽ ሰው ተኮር ተግባር መሆኑን አብራርተዋል። ከማዕድ ማጋራቱ ባለፈም አሁን ላይ በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ግጭትና በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ሊከሰት የሚችለውን ጊዜያዊ የኑሮ ጫና ለማቃለልና የገበያ ጉድለትን ለመሙላት መንግስት ከፍተኛ በጀት መድቦ መሰረታዊ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በዚህም የምርት እጥረት እንዳያጋጥም በተሰራው ስራ በከተማዋ የተረጋጋ የገበያ ሁኔታ እንዲሰፍን መደረጉንም ነው የገለጹት። እነዚህ ወቅታዊ ችግሮችን ለመሻገር የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ ከለውጡ ወዲህ የተጀመሩ የሰው ተኮር ስራዎች አካል መሆናቸውን የገለጹት ከንቲባዋ፤ አዲስ አበባ ለሀብታሙም ለድሃውም እኩል የተመቸች እንድትሆንና ስራዎቻቸው ማንንም ያልዘነጉ አካታች እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በከተማዋ እየታየ ያለው ልማት በሰዉ ኑሮና አኗኗር ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ አመልክተዋል። መስጠት አያጎድልም በሚል የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው ለተባበሩ ልበ ቀና ባለሀብቶችና ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች በጉልበታቸው በበጎ ፈቃደኝነት እያገለገሉ ላሉ ወጣቶች በራሳቸውና በነዋሪዎች ስም ምስጋና አቅርበዋል። በተለይም በዛሬው ዕለት በከንቲባ ፅህፈት ቤት ለቀረበው ማዕድ ማጋራት ጆስፖንግ ትሬዲንግ (Jospong Trading) 15 ሚሊዮን ብር፣ አቶ ጀማል (ሚድሮክ) 10 ሚሊዮን ብር፣ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን 7 ሚሊዮን ብር፣ አቶ በላይነህ ክንዴ (BKG) 5 ሚሊዮን ብር፣ አትሌት ዮሐንስ ቢፋ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር እንዲሁም አቶ ተካበ ሙሉ 500 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረጋቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የትንሳኤ በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ መዳን ፍቅሩን እስከ መስቀል የገለጸበት በመሆኑ፣ ነዋሪዎች በዓሉን ሲያከብሩ በታላቅ ፍቅርና መተሳሰብ መሆን እንዳለበት አሳስበዋል። ሁሉም ዜጋ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ያለውን አጋርነት በተግባር በመግለጽ አንዱ ለሌላው የደስታ፣ የሰላምና የአብሮነት ምክንያት እንዲሆን በመመኘት በራሳቸውና በከተማ አስተዳደሩ ስም መልካም የበዓል ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ከተሞችን ምቹ ፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል-አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)
Apr 8, 2026 41
ባሕር ዳር፤መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦ከተሞችን ለመኖሪያ ምቹ፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው የማድረግ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በአማራ ክልል በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ክልል የከተማ ዘርፍ ተቋማት የ2018 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)፤ ከተሞችን ምቹ፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው የማድረግ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የ25 ዓመታት አሻጋሪና ዘላቂ የልማት ዕቅድ ታቅዶ ወደ ሥራ በመገባቱ በበጀት አመቱ ጥሩ አፈፃፀም መታየቱን ገልጸው፤ በቀጣይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በከተሞች የኮሪደር ልማት ከውበትም ባሻገር የዘመናዊ ከተሞችን ግንባታ መሰረት እያኖረ መሆኑን አንስተው፤ ምቹ ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው ስማርት ከተሞችን የመገንባት ስራ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የነቃ ተሳትፎ ሊያደርግ ይገባል
Apr 8, 2026 73
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የአምራች ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ በትጋት መሥራት እንዳለበት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባካሄደው 9ኛው ጠቅላላ ጉባኤ፣ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድን ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል። በምክትል ፕሬዝዳንትነት ደግሞ ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ የተመረጡ ሲሆን፣ ጉባኤው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫንም በስኬት አጠናቋል። በጉባኤው ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል፣ መንግሥት አምራች ኢንዱስትሪው በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጉልህ ሚና እንዲኖረው ለማስቻል መሰረት የሚጥሉ ተግባራት እያከናወነ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካትና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል ነው ያሉት። መንግሥት ለአምራች ኢንዱስትሪው ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ መሆኑን በማንሳት፥ ይህን ለማስፋት ምክር ቤቱ በሂደቱ ግብዓት የመስጠትና የነቃ ተሳትፎ የማድረግ ኃላፊነት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በአምራች ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተደራጀ መንገድ ለመንግሥት በማቅረብና በፖሊሲ ግብዓቶች ላይ በንቃት በመሳተፍ የዘርፉን ተወዳዳሪነት እንዲያረጋግጥ አጽንኦት ሰጥተዋል። መንግሥት ለአምራች ዘርፉ ምቹ የሥራ አውድ ለመፍጠር የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያዎችን ማድረጉን ጠቅሰው፣ ዘርፉ በወጪ ንግድና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ አወንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። አዲሱ የምክር ቤት አመራር ተኪ ምርትን በማስፋት፣በሥራ ዕድል ፈጠራና ወጪ ንግድ ላይ አምራች ኢንዱስትሪው በላቀ ሁኔታ እንዲሠራ የማድረግ ሃላፊነቱን እንዲወጣ አስገንዝበዋል። አዲሱ የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው፣ ምክር ቤቱ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር ተቀራርቦ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ምርት እንዲኮሩ ግንዛቤ ማስረጽ፣ የኢትዮጵያን የወጪ ንግድ ምርቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ማድረግ፣ ከዘርፉ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ከመንግሥት ጋር በመሆን በዘላቂነት መፍታት ላይ በትጋት ይሠራል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አበባየሁ ግርማ፤የምክር ቤቱ አመራሮች ምርጫ ዲሞክራሲያዊነቱን ጠብቆ የተካሄደና ስኬታማ መሆኑን አንስተዋል። ምክር ቤቱ በተለይ በከፍተኛ አምራቾች በአነስትኛ ኢንዱስትሪዎች መካከል የልምድና የቴክኖሎጂ ልውውጥን በማስፋት ረገድ በትኩረት እንዲሠራ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 80 ዓመታት የዕድገትና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ ቀጥሏል
Apr 8, 2026 105
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 80 ዓመታት የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለፁ። አየር መንገዱ ፈተናዎች በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡንም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የአየር መንገዱ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው፤ ተቋሙ ባለፋት ስምንት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያ የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን ገልጸዋል። አየር መንገዱ የመጀመሪያ በረራውን መጋቢት 30 ቀን 1938 ዓ.ም ማድረጉን ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በነበሩት ዓመታት ባስመዘገበው ተከታታይ ዕድገት በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ 145 መዳረሻዎች ያሉት ግዙፍ አየር መንገድ ለመሆን መብቃቱን ተናግረዋል። አየር መንገዱ ዘመኑ ያፈራቸውን እጅግ ዘመናዊ አውሮፕላኖች በመጠቀም ለደንበኞቹ የላቀ አገልግሎት እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ በተለይም በተቋም ግንባታ ረገድ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት የራሱን አውሮፕላኖች ጥገና ማከናወን የሚያስችል ሙሉ አቅም የፈጠረ ሲሆን ይህም ለኩባንያው ዘላቂ ዕድገት ትልቅ መሠረት መጣሉን አመላክተዋል። የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ለማፍራት የራሱ አቪዬሽን አካዳሚ ያለው አየር መንገዱ፥ የአፍሪካ ትልቁን የአቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በመገንባት በታሪኩ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው ስኬት ማስመዝገቡን ገልጸዋል። አየር መንገዱ ራዕዩን መሸከም የሚችል ብቁ የሰው ኃይል ማፍራት እና የሥራ ሥነ-ምግባር ያለው ታታሪ ሠራተኛ በመፍጠር ረገድ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል። የካርጎ የጭነት አገልግሎት አቅሙን ከማሳደጉም በላይ በርካታ ደጋፊ መሠረተ ልማቶችን ገንብቷል ብለዋል። እነዚህ የተቀናጁ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችና የደንበኞችን እርካታ ታሳቢ ያደረጉ አሰራሮች አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የገበያ ውድድር ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥልና አስተማማኝ ዕድገት እንዲያስመዘግብ አስችለውታል ነው ያሉት። አየር መንገዱ 150 አውሮፕላኖች ያሉት ሲሆን የበረራ ተደራሽነቱንና ጥራቱን ይበልጥ ለማሳደግ 117 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለመግዛት በሂደት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። ያለፉት ሰማንያ ዓመታት ለአየር መንገዱ የታታሪነት፣ የጠንክሮ መስራት እና የስኬት ዘመናት መሆናቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገጠሙትን ፈተናዎች በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡን ጠቅሰዋል።
ፖለቲካ
የክልሉን ሰላም ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Apr 8, 2026 30
ባህር ዳር፤መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በተሰራው የተቀናጀ የህግ ማስከበር ስራ የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፥ የክልሉን ሰላም ለማዝለቅ የተቀናጀ የፀጥታ ማስከበር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ለዚህም የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሎች ከሌሎች የፀጥታ አባላት ጋር በመተባበር የፀጥታ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ባለፉት ጊዜያት በክልሉ የተከሰተው የሰላም እጦት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና መፍጠሩን አንስተው፤መንግስት ችግሩን በመነጋገር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሰፊ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ታጥቀው ጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭን በመቀበል ወደ ሰላማዊ ኑሮ እየመጡ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የክልሉ ህዝብ ሰላምና ልማት አጥብቆ ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ የሰላምን አማራጭ ባልተከተሉ ቡድኖች ላይ የፀጥታ ሃይሉ ህግና ስርዓት የማስከበር ስራውን ህብረተሰቡን ባሳተፈ አግባብ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አክለዋል። የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሉ መጭው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ስጋት መከናወን እንዲችል ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሆነ አስገንዝበዋል። የትንሳኤ በዓልም በሰላም እንዲከበር የተቀናጀ ስምሪት ተሰጥቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመዋል። በበዓል አከባበሩ ወቅት ህብረተሰቡ ማንኛውንም አጠራጣሪ ሁኔታ ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ ሃይል ጥቆማ በመስጠት የሰላሙ ባለቤት መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የዜግነት ክብር መገለጫ ነው
Apr 8, 2026 339
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የዜግነት ክብር መገለጫ መሆኑን አባትና እናት አርበኞች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ሲያካሂድ ቆይቷል። በተጨማሪም ቦርዱ የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሟል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስቻለቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ባህል በመገንባት የሀገር ፍቅርና ክብር የሚገለፅበት የዜጎች የጋራ መድረክ ነው ብለዋል። አባት አርበኛ ባሻ ሽመልስ ወልደ-ተክሌ፤ በኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ካርድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። ዜጎችም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ተጨማሪ የድምፅ መስጫ ካርድ ማውጫ ጊዜን በመጠቀም ካርድ መውሰድ እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄድ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞከራሲ ባህል በመገንባት የዜግነት ክብር መገለጫ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ዜጎች ይበጀናል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት ከወዲሁ በመዘጋጀት ለሀገራቸው ያላቸውን ክብር ማሳየት እንደሚኖርባቸው አንስተዋል። ሌላኛው አባት አርበኛ ኮሎኔል አያሌው በላይ፤ ምርጫ የዜግነት ክብር መገለጫና ሕገ-መንግስታዊ የመምረጥና መመረጥ መብት ማረጋገጫ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ለመገንባት አንዱ መሳሪያ ነው ያሉት አባት አርበኛ ኮሎኔል አያሌው፤ የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ለማጠናከር የምርጫ ተሳትፎ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል። በዚህም በምርጫ ሂደት ድምፅ ለመስጠት ዕድሜው የሚፈቅድለት ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ በማውጣት ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀት እንዳለበት አስረድተዋል። እናት አርበኛ አልማዝ አንበርብር በበኩላቸው፤ ምርጫ የሀገርን ልማትና ዕድገት ለማስቀጠል ዜጎች በአደባባይ የሚሳተፉበት የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሁሉም ዜጋ ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በማውጣት ለሀገሩ ያለውን ክብር በምርጫ ተሳትፎ ማሳየት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዜጎች የመምረጥና መመረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ይበጀናል ለሚሉት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሌ/ጄ ታደሰ ወረደን ሹመት ለአንድ ዓመት አራዘሙ
Apr 8, 2026 242
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደን ሹመት ለአንድ ዓመት አራዝመዋል፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 62(9) እና በዐዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀፅ 2(ለ) መሠረት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደርን በርዕሰ መስተዳድርነት እንዲመሩ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር አስመልክቶ በጸደቀው ደንብ ቁጥር 479/2013 አንቀጽ 4(2) እና የዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ባቀረቡት መሠረት ነው የሹመት ጊዜያቸው የተራዘመው።
የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለአምራች ኃይል ግንባታ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 7, 2026 1548
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለአምራች ኃይል ግንባታ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ስኬት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ይህም በተለይ ለጀርባ አጥንት ለሆነው አምራች እና ተመራማሪ ኃይል ግንባታ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በበይነ መረብ ባካሄዱት ውይይት፤ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን፣ የሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የጤና መድህን፣ የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲ እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ የ2018 ዓ.ም የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀምን ገምግመዋል። በዚሁ መድረክ በፌዴራል ደረጃ የተከለሰውን የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ የጸደቀ ሲሆን፣ በእቅዱ የተመለከቱ ቁልፍ ተግባራት በሁሉም የሴክተር መስሪያ ቤቶች እና የክልል ቢሮዎች ተካተው ተግባራዊ እንዲሆኑም መመሪያ ሰጥተዋል። የሰቆጣ ቃል ኪዳን ትግበራን በተመለከተ፣ ኢትዮጵያ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሷን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የ15 ዓመቱ ፍኖተ ካርታ አካል የሆነውን የመጨረሻውን የአምስት ዓመት የማስፋት ምዕራፍ (ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም) የትግበራ እቅድ መጽደቁን ይፋ አድርገዋል። በዚህም የመቀንጨር እና ሌሎች የስርዓተ ምግብ ችግሮችን በፍጥነት ለመቀነስ እስከ አሁን የተገኙ ልምዶችን በመቀመር ማህበረሰቡን በባለቤትነት ማሳተፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። ከዚህ በተጨማሪም የፌዴራል የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ምክር ቤትን ለማቋቋም በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የባለድርሻ አካላት ግብዓት ተካቶበት ወደ ቀጣይ አፈጻጸም እንዲሸጋገር አቅጣጫ ተቀምጧል። የጤና መድህን አገልግሎትን ይበልጥ ለማጠናከርም በክልል ደረጃ ጠንካራ አስፈጻሚ አካላትን ማደራጀትና በያዝነው ዓመት የፌዴራል ቋት (Pool) መመስረት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ስምምነት ላይ መደረሱንም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት። የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ውጤታማነትን ለማስቀጠልም፣ ዜጎች እንደ መክፈል አቅማቸው መዋጮ የሚያደርጉበት አሰራር መጠናከር እንዳለበትም አመልክተዋል። ፕሮግራሙ ያለው ለሌለው የሚደጋገፍበት ወሳኝ ስርአት በመሆኑም፣ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲ እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ ፍኖተ ካርታን በተመለከተ፣ ቀጣይ የ5 ዓመታት ትግበራዎች በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ እንዲመሩ መወሰኑን ጠቁመዋል። ለዚህም በፌዴራል እና በክልል ደረጃ ለፕሮግራሙ ልዩ ትኩረት በመስጠት በቂ በጀት እንዲመደብና ከተለያዩ ምንጮች የሀብት ማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
አዋጁ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ጉዞን ለማፋጠን ትልቅ ዐቅም ይፈጥራል
Apr 7, 2026 606
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፡- የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አዋጅ የዘርፉን ትራንስፎርሜሽንና ምርታማነት ለማሳደግ ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ "የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ" ላይ የውሳኔ ሐሳብ ካቀረበ በኋላ ምክር ቤቱ መርምሮ አዋጁን ቁጥር 1411/2018 አድርጎ አጽድቋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ የውሳኔ ሐሳቡን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ አዋጁ በመንግሥት ብቻ ተወስኖ የቆየውን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ወደ ባለብዙ ተዋንያን ሥርዓት የሚቀይር ነው። ይህም በዘርፉ የግል ባለሀብቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ሌሎች አካላት በሕጋዊ መንገድ እንዲሳተፉ በር ይከፍታል ብለዋል። አዋጁ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና ዲጂታል አሠራሮችን ለአርሶአደሩ ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም አገልግሎት ሰጪዎች በብቃት ማረጋገጫና በምዝገባ ሥርዓት ውስጥ እንዲያልፉ በማድረግ ፍትሐዊና ጥራት ያለው አገልግሎት ማረጋገጥ ያስችላል ነው ያሉት። የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፤ አዋጁ ሀገር በቀል ዕውቀትን ከሳይንሳዊ መንገድ ጋር በማዳበር የግብርና ትራንስፎርሜሽኑን ለማሳለጥ ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ሀገራዊ ለውጡ ዜጎች በሀገራቸው ያላቸው ተስፋና እምነት እንዲለመልም አድርጓል
Apr 7, 2026 672
ጂንካ፤መጋቢት 29/2018(ኢዜአ):- ሀገራዊ ለውጡ ዜጎች በሀገራቸው ያላቸው ተስፋና እምነት እንዲለመልም ማድረጉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለፁ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተለያዩ ከተሞች ሀገራዊ ለውጡን የሚዘክር ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄዷል ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በጂንካ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ያለፉት ስምንት ዓመታትን ‹‹በፈተናዎች የታጀቡ ነገር ግን በስኬት የተቋጩ›› ሲሉ ገልፀዋቸዋል። በሀገራዊ ለውጡ በፖለቲካው ምህዳር አንዱ ቤተኛ ሌላው አጋር የሚሆንበት የፖለቲካ አውድ ተቀይሮ ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እኩል ውሳኔ የሚሰጡበት አውድ ተፈጥሯል ነው ያሉት። በዚህም ሀገራዊ ለውጡ ዜጎች በሀገራቸው ያላቸው ተስፋና እምነት እንዲለመልም አድርጓል ብለዋል። ሀገራዊ ለውጡ አሳሪ የሆነ የፖለቲካ ባህል ተቀይሮ በምትኩ ነፃ፣ አሳታፊ፣ አካታችና የሀሳብ ልዩነቶችን ያከበረ የፖለቲካ ምህዳር የተፈጠረበት መሆኑንም አንስተዋል። በሀገራዊ ለውጡ ልመናን የሚፀየፍ ትውልድ መፈጠሩን ገልፀው፥ ትውልዱ የእርዳታ ስንዴን መቀበል ሳይሆን አምርቶ ወደ ውጭ መላክን ተምሯል ነው ያሉት። የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ በበኩላቸው ሀገራዊ ለውጡ አካታችና ለህብረ ብሔራዊ አንድነት እውቅናን የሰጠ ስለመሆኑመ አንስተዋል። በሀገራዊ ለውጡ ዜጎች ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸው ተከብሮ ፍትሀዊ ተጠቃሚነታቸው መረጋገጡን አመልክተዋል። በለውጡ ዓመታትም ጂንካን እናልማ በሚል መሪ ሀሳብ ህዝቡን በማሳተፍ በከተማዋ የተጀመሩ የኮሪደርና የመልሶ ማልማት ስራዎች ተጨባጭ ለውጦች ማምጣት ችለዋል ያሉት ደግሞ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ደግፌ ጌታቸው ናቸው። የጂንካ ከተማ በለውጡ ዓመታት ባገኘችው የመልማት እድል ፈጣን እድገት በማሳየት ላይ መሆኗንም ጠቁመዋል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ የተሳተፉት የጂንካ ከተማ ነዋሪው አቶ ሳሙኤል ጎታ እና ሰላም ኃይሌ፥ ሀገራዊ ለውጡ ከጨለማ ወደ ብርሃን የተሸጋገርንበት ነው ብለዋል። በሀገራዊ ለውጡ በሀገራችን ላይ ያለን እምነት እና ተስፋ ለምልሟል ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ፥ ይህንን ለውጥ ለማስቀጠልም ሁለንተናዊ ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በጂንካ ከተማ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይም ለሀገራዊ ለውጡ እውቅና የሚሰጡ በርካታ መልእክቶች ተላልፈዋል ።
የለውጡ መንግስት አሰባሳቢ ትርክትን የመገንባት ተግባር በትኩረት አከናውኗል
Apr 7, 2026 776
ወላይታ ሶዶ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጡ መንግስት አካታች የፖለቲካ ምህዳርን በመፍጠር አሰባሳቢ ትርክትን የመገንባት ተግባርን በትኩረት ማከናወኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ አመለከቱ። የሀገራዊ ለውጡን 8ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለተገኘው ስኬት እውቅና የሚሰጥ የድጋፍ ሰልፍ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ ዛሬ ተካሄዷል። በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጡ ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ዜጎችንና ሀገሪቱን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች ተመዝግበዋል። መጋቢት 24 በሀገራችን ታሪክ የፖለቲካ ለውጥ የተደረገበትና አዲስ አተያይ እውን የተደረገበት ዕለት መሆኑንም ገልጸዋል። የለውጡ መንግስት 8ተኛ ዓመትን ስናከብር በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠል ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡ የለውጡ መንግስት አካታች የፖለቲካ ምህዳር በመፍጠር በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታና ገዢ ትርክትን የመገንባት ስራ በትኩረት መስራቱንም ገልጸዋል። ለኢኮኖሚ ዕድገት ምሰሶ የሆኑ ዘርፎችን በመለየት በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች መታየታቸውን የገለጹት ዋና ተጠሪው አንድነታችንን በማጠናከር የተመዘገቡ ድልና ስኬቶችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡ የመጋቢት 24 ድል ለትውልድ ታሪክ፣ ለሀገር ደግሞ አዲስ ተስፋን የወለደ ቀን መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ናቸው። በለውጡ ዓመታት የሀገር ሉዓላዊነትን የማስጠበቅና ሀገርን የመገንባት ራዕይ እውን የሚያደርጉ ሥራዎች መሰራታቸውንም ገልጸዋል። መጋቢት 24 አካታችና ኅብረ-ብሔራዊ የፖለቲካ ስርዓት ግንባታ መሠረት የተጣለበት መሆኑን ጠቅሰው በሁሉም ዘርፍ የተመዘገቡ አመርቂ ውጤቶች የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል፡፡ እንደ ዞን በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል በትብብር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማርያም በበኩላቸው፤ መጋቢት 24 መንግስት ሀገርን ከመበታተን በመታደግ የለውጡ ጉዞ እንዲቀጣጠል ያደረገበት ነው ብለዋል፡፡ የወላይታ ሶዶ ከተማም የትሩፋቱ ተቋዳሽ በመሆኑ የአስፋልት መንገድ ግንባታ፣ የኮሪደር ልማት እና ሌሎች በርካታ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በከተማው የተጀመረውን የለውጥ ተምሳሌት ስራዎችን ለማስቀጠል የከተማ አሰተዳደሩ ከነዋሪዎች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ተናግረው ህዝቡም ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።
በጠቅላላ ምርጫው የሴቶችን ተሳትፎ ማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Apr 7, 2026 636
አዳማ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ መሆኑን የሲቪክ ማኅበራት አስታወቁ። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ትዕግሥት ተረፈ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ፌዴሬሽኑ ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው። በተለይም ሴቶች በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን አመልክተዋል። ሴቶች የሀገሪቱን ቀጣይ አቅጣጫ በመወሰን ረገድ ያላቸውን የላቀ ሚና በመጠቀም፣ ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ እንዲመርጡ የማንቃት ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ የሚጎትቱ ችግሮችን ለመፍታትም ለቅንጅታዊ አሠራር ትኩረት መሰጠቱን አስረድተዋል። የምርጫው በስኬት መጠናቀቅ ለሀገር ሰላምና ለዲሞክራሲ ባህል መጎልበት ያለው ሚና ወሳኝ በመሆኑ፣ ለተግባራዊነቱ ፌዴሬሽኑ በትጋት እየሠራ እንደሚገኝም ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ፌዴሬሽን ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ እጸገነት ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ዲሞክራሲያዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት እንዲሳተፉ ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ሴቶች በምርጫው በመራጭነት፣ በተመራጭነትና በታዛቢነት እንዲሳተፉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኦሮሚያ አካል ጉዳተኞች ማኅበራት ፌዴሬሽን አመራር ወይዘሮ ጀሚላ አብደላ፤ በክልሉ የሚገኙ አካል ጉዳተኞች በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። አካል ጉዳተኞች ለሀገር ልማትና ሰላም የተሻለ አማራጭ የያዘን የፖለቲካ ፓርቲ እንዲመርጡ ግንዛቤ እየተፈጠረ መሆኑንም ጠቁመዋል። በተለይም አካል ጉዳተኛ ሴቶች በመራጭነት፣ በእጩ ተወዳዳሪነት እንዲሁም በታዛቢነት በመሳተፍ የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ምቹ ምኅዳር መፈጠሩን አድንቀዋል።
ፖለቲካ
የክልሉን ሰላም ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Apr 8, 2026 30
ባህር ዳር፤መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በተሰራው የተቀናጀ የህግ ማስከበር ስራ የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፥ የክልሉን ሰላም ለማዝለቅ የተቀናጀ የፀጥታ ማስከበር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ለዚህም የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሎች ከሌሎች የፀጥታ አባላት ጋር በመተባበር የፀጥታ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ባለፉት ጊዜያት በክልሉ የተከሰተው የሰላም እጦት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና መፍጠሩን አንስተው፤መንግስት ችግሩን በመነጋገር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሰፊ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ታጥቀው ጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭን በመቀበል ወደ ሰላማዊ ኑሮ እየመጡ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የክልሉ ህዝብ ሰላምና ልማት አጥብቆ ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ የሰላምን አማራጭ ባልተከተሉ ቡድኖች ላይ የፀጥታ ሃይሉ ህግና ስርዓት የማስከበር ስራውን ህብረተሰቡን ባሳተፈ አግባብ አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አክለዋል። የክልሉ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይሉ መጭው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ስጋት መከናወን እንዲችል ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሆነ አስገንዝበዋል። የትንሳኤ በዓልም በሰላም እንዲከበር የተቀናጀ ስምሪት ተሰጥቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመዋል። በበዓል አከባበሩ ወቅት ህብረተሰቡ ማንኛውንም አጠራጣሪ ሁኔታ ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ ሃይል ጥቆማ በመስጠት የሰላሙ ባለቤት መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የዜግነት ክብር መገለጫ ነው
Apr 8, 2026 339
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የዜግነት ክብር መገለጫ መሆኑን አባትና እናት አርበኞች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ሲያካሂድ ቆይቷል። በተጨማሪም ቦርዱ የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሟል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስቻለቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ባህል በመገንባት የሀገር ፍቅርና ክብር የሚገለፅበት የዜጎች የጋራ መድረክ ነው ብለዋል። አባት አርበኛ ባሻ ሽመልስ ወልደ-ተክሌ፤ በኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ካርድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። ዜጎችም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ተጨማሪ የድምፅ መስጫ ካርድ ማውጫ ጊዜን በመጠቀም ካርድ መውሰድ እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄድ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞከራሲ ባህል በመገንባት የዜግነት ክብር መገለጫ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ዜጎች ይበጀናል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት ከወዲሁ በመዘጋጀት ለሀገራቸው ያላቸውን ክብር ማሳየት እንደሚኖርባቸው አንስተዋል። ሌላኛው አባት አርበኛ ኮሎኔል አያሌው በላይ፤ ምርጫ የዜግነት ክብር መገለጫና ሕገ-መንግስታዊ የመምረጥና መመረጥ መብት ማረጋገጫ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ለመገንባት አንዱ መሳሪያ ነው ያሉት አባት አርበኛ ኮሎኔል አያሌው፤ የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ለማጠናከር የምርጫ ተሳትፎ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል። በዚህም በምርጫ ሂደት ድምፅ ለመስጠት ዕድሜው የሚፈቅድለት ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ በማውጣት ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀት እንዳለበት አስረድተዋል። እናት አርበኛ አልማዝ አንበርብር በበኩላቸው፤ ምርጫ የሀገርን ልማትና ዕድገት ለማስቀጠል ዜጎች በአደባባይ የሚሳተፉበት የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሁሉም ዜጋ ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በማውጣት ለሀገሩ ያለውን ክብር በምርጫ ተሳትፎ ማሳየት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዜጎች የመምረጥና መመረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ይበጀናል ለሚሉት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሌ/ጄ ታደሰ ወረደን ሹመት ለአንድ ዓመት አራዘሙ
Apr 8, 2026 242
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደን ሹመት ለአንድ ዓመት አራዝመዋል፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 62(9) እና በዐዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀፅ 2(ለ) መሠረት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደርን በርዕሰ መስተዳድርነት እንዲመሩ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር አስመልክቶ በጸደቀው ደንብ ቁጥር 479/2013 አንቀጽ 4(2) እና የዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ባቀረቡት መሠረት ነው የሹመት ጊዜያቸው የተራዘመው።
የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለአምራች ኃይል ግንባታ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 7, 2026 1548
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለአምራች ኃይል ግንባታ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ስኬት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ይህም በተለይ ለጀርባ አጥንት ለሆነው አምራች እና ተመራማሪ ኃይል ግንባታ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በበይነ መረብ ባካሄዱት ውይይት፤ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን፣ የሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የጤና መድህን፣ የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲ እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ የ2018 ዓ.ም የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀምን ገምግመዋል። በዚሁ መድረክ በፌዴራል ደረጃ የተከለሰውን የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ የጸደቀ ሲሆን፣ በእቅዱ የተመለከቱ ቁልፍ ተግባራት በሁሉም የሴክተር መስሪያ ቤቶች እና የክልል ቢሮዎች ተካተው ተግባራዊ እንዲሆኑም መመሪያ ሰጥተዋል። የሰቆጣ ቃል ኪዳን ትግበራን በተመለከተ፣ ኢትዮጵያ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሷን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የ15 ዓመቱ ፍኖተ ካርታ አካል የሆነውን የመጨረሻውን የአምስት ዓመት የማስፋት ምዕራፍ (ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም) የትግበራ እቅድ መጽደቁን ይፋ አድርገዋል። በዚህም የመቀንጨር እና ሌሎች የስርዓተ ምግብ ችግሮችን በፍጥነት ለመቀነስ እስከ አሁን የተገኙ ልምዶችን በመቀመር ማህበረሰቡን በባለቤትነት ማሳተፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። ከዚህ በተጨማሪም የፌዴራል የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ምክር ቤትን ለማቋቋም በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የባለድርሻ አካላት ግብዓት ተካቶበት ወደ ቀጣይ አፈጻጸም እንዲሸጋገር አቅጣጫ ተቀምጧል። የጤና መድህን አገልግሎትን ይበልጥ ለማጠናከርም በክልል ደረጃ ጠንካራ አስፈጻሚ አካላትን ማደራጀትና በያዝነው ዓመት የፌዴራል ቋት (Pool) መመስረት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ስምምነት ላይ መደረሱንም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት። የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ውጤታማነትን ለማስቀጠልም፣ ዜጎች እንደ መክፈል አቅማቸው መዋጮ የሚያደርጉበት አሰራር መጠናከር እንዳለበትም አመልክተዋል። ፕሮግራሙ ያለው ለሌለው የሚደጋገፍበት ወሳኝ ስርአት በመሆኑም፣ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲ እና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ ፍኖተ ካርታን በተመለከተ፣ ቀጣይ የ5 ዓመታት ትግበራዎች በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ እንዲመሩ መወሰኑን ጠቁመዋል። ለዚህም በፌዴራል እና በክልል ደረጃ ለፕሮግራሙ ልዩ ትኩረት በመስጠት በቂ በጀት እንዲመደብና ከተለያዩ ምንጮች የሀብት ማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
አዋጁ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ጉዞን ለማፋጠን ትልቅ ዐቅም ይፈጥራል
Apr 7, 2026 606
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፡- የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አዋጅ የዘርፉን ትራንስፎርሜሽንና ምርታማነት ለማሳደግ ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ "የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ" ላይ የውሳኔ ሐሳብ ካቀረበ በኋላ ምክር ቤቱ መርምሮ አዋጁን ቁጥር 1411/2018 አድርጎ አጽድቋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ የውሳኔ ሐሳቡን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ አዋጁ በመንግሥት ብቻ ተወስኖ የቆየውን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ወደ ባለብዙ ተዋንያን ሥርዓት የሚቀይር ነው። ይህም በዘርፉ የግል ባለሀብቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ሌሎች አካላት በሕጋዊ መንገድ እንዲሳተፉ በር ይከፍታል ብለዋል። አዋጁ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና ዲጂታል አሠራሮችን ለአርሶአደሩ ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም አገልግሎት ሰጪዎች በብቃት ማረጋገጫና በምዝገባ ሥርዓት ውስጥ እንዲያልፉ በማድረግ ፍትሐዊና ጥራት ያለው አገልግሎት ማረጋገጥ ያስችላል ነው ያሉት። የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፤ አዋጁ ሀገር በቀል ዕውቀትን ከሳይንሳዊ መንገድ ጋር በማዳበር የግብርና ትራንስፎርሜሽኑን ለማሳለጥ ትልቅ ዐቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ሀገራዊ ለውጡ ዜጎች በሀገራቸው ያላቸው ተስፋና እምነት እንዲለመልም አድርጓል
Apr 7, 2026 672
ጂንካ፤መጋቢት 29/2018(ኢዜአ):- ሀገራዊ ለውጡ ዜጎች በሀገራቸው ያላቸው ተስፋና እምነት እንዲለመልም ማድረጉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለፁ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተለያዩ ከተሞች ሀገራዊ ለውጡን የሚዘክር ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄዷል ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በጂንካ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ያለፉት ስምንት ዓመታትን ‹‹በፈተናዎች የታጀቡ ነገር ግን በስኬት የተቋጩ›› ሲሉ ገልፀዋቸዋል። በሀገራዊ ለውጡ በፖለቲካው ምህዳር አንዱ ቤተኛ ሌላው አጋር የሚሆንበት የፖለቲካ አውድ ተቀይሮ ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እኩል ውሳኔ የሚሰጡበት አውድ ተፈጥሯል ነው ያሉት። በዚህም ሀገራዊ ለውጡ ዜጎች በሀገራቸው ያላቸው ተስፋና እምነት እንዲለመልም አድርጓል ብለዋል። ሀገራዊ ለውጡ አሳሪ የሆነ የፖለቲካ ባህል ተቀይሮ በምትኩ ነፃ፣ አሳታፊ፣ አካታችና የሀሳብ ልዩነቶችን ያከበረ የፖለቲካ ምህዳር የተፈጠረበት መሆኑንም አንስተዋል። በሀገራዊ ለውጡ ልመናን የሚፀየፍ ትውልድ መፈጠሩን ገልፀው፥ ትውልዱ የእርዳታ ስንዴን መቀበል ሳይሆን አምርቶ ወደ ውጭ መላክን ተምሯል ነው ያሉት። የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ በበኩላቸው ሀገራዊ ለውጡ አካታችና ለህብረ ብሔራዊ አንድነት እውቅናን የሰጠ ስለመሆኑመ አንስተዋል። በሀገራዊ ለውጡ ዜጎች ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸው ተከብሮ ፍትሀዊ ተጠቃሚነታቸው መረጋገጡን አመልክተዋል። በለውጡ ዓመታትም ጂንካን እናልማ በሚል መሪ ሀሳብ ህዝቡን በማሳተፍ በከተማዋ የተጀመሩ የኮሪደርና የመልሶ ማልማት ስራዎች ተጨባጭ ለውጦች ማምጣት ችለዋል ያሉት ደግሞ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ደግፌ ጌታቸው ናቸው። የጂንካ ከተማ በለውጡ ዓመታት ባገኘችው የመልማት እድል ፈጣን እድገት በማሳየት ላይ መሆኗንም ጠቁመዋል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ የተሳተፉት የጂንካ ከተማ ነዋሪው አቶ ሳሙኤል ጎታ እና ሰላም ኃይሌ፥ ሀገራዊ ለውጡ ከጨለማ ወደ ብርሃን የተሸጋገርንበት ነው ብለዋል። በሀገራዊ ለውጡ በሀገራችን ላይ ያለን እምነት እና ተስፋ ለምልሟል ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ፥ ይህንን ለውጥ ለማስቀጠልም ሁለንተናዊ ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በጂንካ ከተማ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይም ለሀገራዊ ለውጡ እውቅና የሚሰጡ በርካታ መልእክቶች ተላልፈዋል ።
የለውጡ መንግስት አሰባሳቢ ትርክትን የመገንባት ተግባር በትኩረት አከናውኗል
Apr 7, 2026 776
ወላይታ ሶዶ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጡ መንግስት አካታች የፖለቲካ ምህዳርን በመፍጠር አሰባሳቢ ትርክትን የመገንባት ተግባርን በትኩረት ማከናወኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ አመለከቱ። የሀገራዊ ለውጡን 8ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለተገኘው ስኬት እውቅና የሚሰጥ የድጋፍ ሰልፍ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ ዛሬ ተካሄዷል። በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጡ ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ዜጎችንና ሀገሪቱን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች ተመዝግበዋል። መጋቢት 24 በሀገራችን ታሪክ የፖለቲካ ለውጥ የተደረገበትና አዲስ አተያይ እውን የተደረገበት ዕለት መሆኑንም ገልጸዋል። የለውጡ መንግስት 8ተኛ ዓመትን ስናከብር በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠል ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡ የለውጡ መንግስት አካታች የፖለቲካ ምህዳር በመፍጠር በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታና ገዢ ትርክትን የመገንባት ስራ በትኩረት መስራቱንም ገልጸዋል። ለኢኮኖሚ ዕድገት ምሰሶ የሆኑ ዘርፎችን በመለየት በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች መታየታቸውን የገለጹት ዋና ተጠሪው አንድነታችንን በማጠናከር የተመዘገቡ ድልና ስኬቶችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡ የመጋቢት 24 ድል ለትውልድ ታሪክ፣ ለሀገር ደግሞ አዲስ ተስፋን የወለደ ቀን መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ናቸው። በለውጡ ዓመታት የሀገር ሉዓላዊነትን የማስጠበቅና ሀገርን የመገንባት ራዕይ እውን የሚያደርጉ ሥራዎች መሰራታቸውንም ገልጸዋል። መጋቢት 24 አካታችና ኅብረ-ብሔራዊ የፖለቲካ ስርዓት ግንባታ መሠረት የተጣለበት መሆኑን ጠቅሰው በሁሉም ዘርፍ የተመዘገቡ አመርቂ ውጤቶች የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል፡፡ እንደ ዞን በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል በትብብር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማርያም በበኩላቸው፤ መጋቢት 24 መንግስት ሀገርን ከመበታተን በመታደግ የለውጡ ጉዞ እንዲቀጣጠል ያደረገበት ነው ብለዋል፡፡ የወላይታ ሶዶ ከተማም የትሩፋቱ ተቋዳሽ በመሆኑ የአስፋልት መንገድ ግንባታ፣ የኮሪደር ልማት እና ሌሎች በርካታ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በከተማው የተጀመረውን የለውጥ ተምሳሌት ስራዎችን ለማስቀጠል የከተማ አሰተዳደሩ ከነዋሪዎች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ተናግረው ህዝቡም ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።
በጠቅላላ ምርጫው የሴቶችን ተሳትፎ ማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Apr 7, 2026 636
አዳማ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ መሆኑን የሲቪክ ማኅበራት አስታወቁ። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ትዕግሥት ተረፈ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ፌዴሬሽኑ ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው። በተለይም ሴቶች በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን አመልክተዋል። ሴቶች የሀገሪቱን ቀጣይ አቅጣጫ በመወሰን ረገድ ያላቸውን የላቀ ሚና በመጠቀም፣ ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ እንዲመርጡ የማንቃት ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ የሚጎትቱ ችግሮችን ለመፍታትም ለቅንጅታዊ አሠራር ትኩረት መሰጠቱን አስረድተዋል። የምርጫው በስኬት መጠናቀቅ ለሀገር ሰላምና ለዲሞክራሲ ባህል መጎልበት ያለው ሚና ወሳኝ በመሆኑ፣ ለተግባራዊነቱ ፌዴሬሽኑ በትጋት እየሠራ እንደሚገኝም ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ፌዴሬሽን ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ እጸገነት ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ዲሞክራሲያዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት እንዲሳተፉ ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ሴቶች በምርጫው በመራጭነት፣ በተመራጭነትና በታዛቢነት እንዲሳተፉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኦሮሚያ አካል ጉዳተኞች ማኅበራት ፌዴሬሽን አመራር ወይዘሮ ጀሚላ አብደላ፤ በክልሉ የሚገኙ አካል ጉዳተኞች በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። አካል ጉዳተኞች ለሀገር ልማትና ሰላም የተሻለ አማራጭ የያዘን የፖለቲካ ፓርቲ እንዲመርጡ ግንዛቤ እየተፈጠረ መሆኑንም ጠቁመዋል። በተለይም አካል ጉዳተኛ ሴቶች በመራጭነት፣ በእጩ ተወዳዳሪነት እንዲሁም በታዛቢነት በመሳተፍ የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ምቹ ምኅዳር መፈጠሩን አድንቀዋል።
ማህበራዊ
የሰው ተኮር ስራዎቻችን ማንንም የማይዘነጉና አካታች ናቸው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Apr 8, 2026 41
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦መንግስት እያከናወናቸው ያሉ የሰው ተኮር ስራዎቻችን ማንንም የማይዘነጉና አካታች ናቸው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች መጪውን የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ ለማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ፣ለአካል ጉዳተኞች፣ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው የአገር ባለውለታ አረጋውያንና በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የመንግስት ሰራተኞች በአጠቃላይ ከ233 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መደረጉን አመልክተዋል። ይህ ተግባር በከተማዋ የማዕከል መስሪያ ቤቶች፣ በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች በስፋት እየተከናወነ ያለ በጎ ተግባር ነው ብለዋል። ከንቲባዋ አክለውም፥ በሁሉም በዓላት የሚደረገው የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር፣ ድጋፍ የሚሹ የከተማዋን ነዋሪዎች ምን ጎደለ? ብሎ በመመልከትና በመጠየቅ ክፍተታቸውን ለመሙላት የሚከናወንና ለነዋሪዎች ያለውን ክብር የሚገልጽ ሰው ተኮር ተግባር መሆኑን አብራርተዋል። ከማዕድ ማጋራቱ ባለፈም አሁን ላይ በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ግጭትና በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ሊከሰት የሚችለውን ጊዜያዊ የኑሮ ጫና ለማቃለልና የገበያ ጉድለትን ለመሙላት መንግስት ከፍተኛ በጀት መድቦ መሰረታዊ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በዚህም የምርት እጥረት እንዳያጋጥም በተሰራው ስራ በከተማዋ የተረጋጋ የገበያ ሁኔታ እንዲሰፍን መደረጉንም ነው የገለጹት። እነዚህ ወቅታዊ ችግሮችን ለመሻገር የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ ከለውጡ ወዲህ የተጀመሩ የሰው ተኮር ስራዎች አካል መሆናቸውን የገለጹት ከንቲባዋ፤ አዲስ አበባ ለሀብታሙም ለድሃውም እኩል የተመቸች እንድትሆንና ስራዎቻቸው ማንንም ያልዘነጉ አካታች እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በከተማዋ እየታየ ያለው ልማት በሰዉ ኑሮና አኗኗር ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ አመልክተዋል። መስጠት አያጎድልም በሚል የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው ለተባበሩ ልበ ቀና ባለሀብቶችና ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች በጉልበታቸው በበጎ ፈቃደኝነት እያገለገሉ ላሉ ወጣቶች በራሳቸውና በነዋሪዎች ስም ምስጋና አቅርበዋል። በተለይም በዛሬው ዕለት በከንቲባ ፅህፈት ቤት ለቀረበው ማዕድ ማጋራት ጆስፖንግ ትሬዲንግ (Jospong Trading) 15 ሚሊዮን ብር፣ አቶ ጀማል (ሚድሮክ) 10 ሚሊዮን ብር፣ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን 7 ሚሊዮን ብር፣ አቶ በላይነህ ክንዴ (BKG) 5 ሚሊዮን ብር፣ አትሌት ዮሐንስ ቢፋ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር እንዲሁም አቶ ተካበ ሙሉ 500 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረጋቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የትንሳኤ በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ መዳን ፍቅሩን እስከ መስቀል የገለጸበት በመሆኑ፣ ነዋሪዎች በዓሉን ሲያከብሩ በታላቅ ፍቅርና መተሳሰብ መሆን እንዳለበት አሳስበዋል። ሁሉም ዜጋ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ያለውን አጋርነት በተግባር በመግለጽ አንዱ ለሌላው የደስታ፣ የሰላምና የአብሮነት ምክንያት እንዲሆን በመመኘት በራሳቸውና በከተማ አስተዳደሩ ስም መልካም የበዓል ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ኢትዮጵያ ሁለት ግዙፍ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ክሶችን በድል አጠናቃለች - ፍትሕ ሚኒስቴር
Apr 8, 2026 88
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በወራት ልዩነት ውስጥ የቀረቡባትን ሁለት ግዙፍ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ክሶች በድል ማጠናቀቋን የፍትሕ ሚኒስቴር ገለጸ። የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት መድረክ ያገኘቻቸውን ሁለት ድሎችን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ሀገሪቱ በተከታታይ ያገኘቻቸው እነዚህ ድሎች በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር የካሳ ክፍያ ከማዳን ባለፈ የሀገሪቱን ሉዓላዊ ጥቅም ያስጠበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ፍትሕ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር 943/2008 በተሰጠው ስልጣን መሠረት፣ የሕዝብና የመንግስትን የፍትሐብሔር ጥቅም የማስጠበቅ፣ የፌደራል መንግስት ዋና አማካሪ የመሆን እና በዓለም አቀፍ መድረክ ሀገሪቱ ስትከሰስ የመከላከል ኃላፊነት እንዳለበት አስረድተዋል። ሚኒስቴሩ ዓለም አቀፍ የግልግል ማዕከላት ቢሯቸውን በኢትዮጵያ እንዲከፍቱ ከማድረግ ጀምሮ በውስጥና በውጭ ባለሙያዎች የታገዘ የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። በድል ከተጠናቀቁት ዋና ዋና ክሶች የመጀመሪያው የቱርኩ የኮንስትራክሽን ኩባንያ የሆነው Akgun Insaat Makina Sanayii ve Dis Ticaret Ltd. Sti. የተባለው አቅርቦት ከነበረው በድምሩ ከ500 ሚሊዮን ዶላር በላይ ክስ መሆኑን ተናግረዋል። ኩባንያው በለገዳዲና ድሬ ግድቦች አቅራቢያ የኢንዱስትሪ ዞን ለማልማት ፈቃድ ተሰጥቶት እንደነበር አስታውሰዋል። አካባቢው የአዲስ አበባ የንጹህ ውሃና ምንጭ በመሆኑ የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሕጉ በሚያዘው መሠረት እንዲያቀርብ በተደጋጋሚ ለቀረበለት ጥያቄ ኩባንያው አጥጋቢ ምላሽ ሊሰጥ ባለመቻሉ የኢንቨስትመንት ስራው ወደ ሌላ ምቹ ቦታ እንዲዛወር አማራጭ ቀርቦለት እንደነበር ገልጸዋል። ኩባንያው ግን የቀረበለትን አማራጭ ባለመቀበል የኢንቨስትመንት ጥበቃ መብት ጥሰት ደርሶብኛል በሚል ክስ ማቅረቡን በማውሳት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለዜጎቹ ንጹህ ውሃ የማቅረብ ኃላፊነቱን መወጣቱ በግልግል ችሎቱ ታምኖበት ክሱ ውድቅ ተደርጓል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ተግባር በአከባቢ ጥበቃ ዓለም አቀፍ ህግጋትን ያከበረ እና መንግሥታዊ ሃላፊነቱን እንደተወጣ የሚቆጠር መሆኑን በማመን ክሱ ውድቅ መደረጉንም ገልጸዋል። ሁለተኛው በኔዘርላንድ የተመዘገበው ኩባንያ African Asset Finance Company Holding B.V ወይንም በተለምዶ ኢትዮ ሊዝ እየተባለ የሚጠራው ኩባንያ፣ ሀገራዊ ግዴታዎችን እንዲያከብር የተሰጡትን ማስጠንቀቂያዎች እንደ ኢንቨስትመንት መብት ጥሰት በመቁጠር ከ334 እስከ 400 ሚሊዮን ዶላር በላይ ካሳ ጠይቆ እንደነበር አንስተዋል። በሄግ፣ ኔዘርላንድስ በተካሄደው የቃል ክርክር የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያዎች ባቀረቡት ብርቱ ክርክር በሦስቱም ገለልተኛ ዳኞች ድምፅ ክሱ ውድቅ ሆኗል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ለክርክሩ ያወጣችውን ወጪና ኪሳራ ኩባንያው እንዲከፍል መወሰኑንም ተናግረዋል። ፍትሕ ሚኒስቴር እነዚህን ክሶች ለመከላከል ከውስጥና ከውጭ ባለሙያዎችን በማዋቀር ብርቱ የክርክር ቡድን መገንባቱን ገልጸዋል። ተገቢውን ፋይናንስና ማስረጃ በማሰባሰብ የክርክር አመራር መስጠቱንም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የቀረቡባትን ክሶች ማሸነፏ በሀገሪቱ የኢንቨስትመንት ምህዳር ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይኖር ከማድረግ ባለፈ በመቶ ሚሊዮን ዶላሮች የሚቆጠር ካሳ እንዳትከፍልና የኢኮኖሚ ጫና ውስጥ እንዳትገባ አስችሏታል ብለዋል። ከድሎቹ ዋና ዋና አንድምታዎች መካከልም ታዳጊ ሀገራት ለጥቅማቸው ራሳቸውን ችለው መሟገትና መርታት እንደሚችሉ ማሳየቱ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ክስን እንደ ማስፈራሪያ ለሚጠቀሙ አንዳንድ ባለሀብቶች ሕግ አክባሪነትን ማስተማሩ፣ ኢትዮጵያ የፈረመቻቸውን ስምምነቶች የምታከብርና ለጤናማ ኢንቨስተሮች ምቹ መሆኗን ማረጋገጡን ለአብነት ጠቅሰዋል።
የትንሳዔ በዓልን ተከትሎ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶች አቅርቦት እጥረት እና የዋጋ ንረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል
Apr 7, 2026 360
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የትንሳዔ በዓልን ተከትሎ መሠረታዊና የበዓል የፍጆታ ምርቶች አቅርቦት እጥረት እና የዋጋ ንረት እንዳይከሰት በቂ የዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ። ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ ለትንሳዔ በዓል የተከናወኑ የገበያ ማረጋጋት ስራዎችን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የበዓልና መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረትና እጥረት እንዳይከሰት ለወራት ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል ብለዋል። በዚህም ከተማ አስተዳደሩ ለበዓል የእርድ እንስሳትን ጨምሮ የኢንዱስትሪ እና የግብርና ምርቶች በስፋት ወደ ከተማዋ እንዲገቡ ማድረጉን ገልጸው፤ ትስስሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ምርቶቹ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ የግብርና ምርቶች ገበያ ማዕከላት፣ በባዛሮች፣ በሰንበት ገበያዎች፣ በሸማች ማህበራትና ሌሎች የገበያ ማዕከላት እንደሚገኙ ጠቁመዋል። ከተማ አስተዳደሩ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ተከትሎ የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት በምርቶች አቅርቦት ላይ ጫና እንዳያሳደር የተለያዩ ውሳኔዎችን እንዳሳለፈም ተናግረዋል፡፡ በዚህም በተለይ የበዓል ምርት ይዘው ለሚገቡ ተሽከርካሪዎች ቅድሚያ ነዳጅ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ በመሆኑም ህብረተሰቡ በከተማዋ በሚገኙ የገበያ ማዕከላት፣ ባዛሮች፣ በሰንበት ገበያዎች፣ በሸማች ማህበራትና ሌሎች የገበያ ማዕከላት ምርቶቹን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያገኝ ነው የተናገሩት።
ህገ-ወጥ የእንስሳት እርድ እና ሥጋ ዝውውርን ለመከላከል የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል
Apr 7, 2026 270
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ከበዓላት ጋር ተያይዞ የሚፈጸም ህገ-ወጥ የእንስሳት እርድ እና ሥጋ ዝውውርን ለመከላከል የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል። የአዲስ አበባ የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት፣ የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማኅበር እና የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የትንሳኤ በዓል ዝግጅት አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። የአዲስ አበባ የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፀጋ ለማ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ህገ ወጥ የእንስሳት እርድና ሥጋ ዝውውርን ለመቆጣጠር የዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል፡፡ በበዓል ወቅት የሚቀርብ ሥጋ ደኅንነቱ የተጠበቀ መሆኑን የኮሚሽኑ የህክምና ባለሙያዎች ጥራትና ደህንነቱን የማረጋገጥ ተግባር እንደሚከናውኑ ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አባባ ቄራዎች ድርጅት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል በበኩላቸው፤ ድርጅቱ የእርድ ክፍል ማስፋፋት፣ የውሃ ጉድጓድ እንዲሁም አዳዲስ 10 ተሸከርካሪዎችን ማዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ በተለይም ድርጅቱ ህገ-ወጥ እርድን ለመከላከል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አየለ ሳህሌ እንዳሉት፤ ህገ-ወጥ የእንስሳት ዝውውርንና እርድን ለመከላከል ኮሚቴ በማዋቀር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው። የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ሀላፊ የምስራች ግርማ፤ ባለስልጣኑ አንድ ተቋም በህገ ወጥ መንገድ የከብት እርድ ሲያከናውን ከተገኘ ከ15 ሺህ ብር ቅጣት ጀምሮ እንደ ጥፋቱ ደረጃ የማሸግ እርምጃ እንደሚወስድ ተናግረዋል፡፡
ኢኮኖሚ
ከተሞችን ምቹ ፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል-አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)
Apr 8, 2026 41
ባሕር ዳር፤መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦ከተሞችን ለመኖሪያ ምቹ፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው የማድረግ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በአማራ ክልል በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ክልል የከተማ ዘርፍ ተቋማት የ2018 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)፤ ከተሞችን ምቹ፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው የማድረግ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የ25 ዓመታት አሻጋሪና ዘላቂ የልማት ዕቅድ ታቅዶ ወደ ሥራ በመገባቱ በበጀት አመቱ ጥሩ አፈፃፀም መታየቱን ገልጸው፤ በቀጣይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በከተሞች የኮሪደር ልማት ከውበትም ባሻገር የዘመናዊ ከተሞችን ግንባታ መሰረት እያኖረ መሆኑን አንስተው፤ ምቹ ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥባቸው ስማርት ከተሞችን የመገንባት ስራ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የነቃ ተሳትፎ ሊያደርግ ይገባል
Apr 8, 2026 73
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የአምራች ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ በትጋት መሥራት እንዳለበት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባካሄደው 9ኛው ጠቅላላ ጉባኤ፣ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድን ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል። በምክትል ፕሬዝዳንትነት ደግሞ ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ የተመረጡ ሲሆን፣ ጉባኤው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫንም በስኬት አጠናቋል። በጉባኤው ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል፣ መንግሥት አምራች ኢንዱስትሪው በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጉልህ ሚና እንዲኖረው ለማስቻል መሰረት የሚጥሉ ተግባራት እያከናወነ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካትና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል ነው ያሉት። መንግሥት ለአምራች ኢንዱስትሪው ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ መሆኑን በማንሳት፥ ይህን ለማስፋት ምክር ቤቱ በሂደቱ ግብዓት የመስጠትና የነቃ ተሳትፎ የማድረግ ኃላፊነት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በአምራች ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተደራጀ መንገድ ለመንግሥት በማቅረብና በፖሊሲ ግብዓቶች ላይ በንቃት በመሳተፍ የዘርፉን ተወዳዳሪነት እንዲያረጋግጥ አጽንኦት ሰጥተዋል። መንግሥት ለአምራች ዘርፉ ምቹ የሥራ አውድ ለመፍጠር የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያዎችን ማድረጉን ጠቅሰው፣ ዘርፉ በወጪ ንግድና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ አወንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። አዲሱ የምክር ቤት አመራር ተኪ ምርትን በማስፋት፣በሥራ ዕድል ፈጠራና ወጪ ንግድ ላይ አምራች ኢንዱስትሪው በላቀ ሁኔታ እንዲሠራ የማድረግ ሃላፊነቱን እንዲወጣ አስገንዝበዋል። አዲሱ የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ ጀማል አህመድ በበኩላቸው፣ ምክር ቤቱ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር ተቀራርቦ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ምርት እንዲኮሩ ግንዛቤ ማስረጽ፣ የኢትዮጵያን የወጪ ንግድ ምርቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ማድረግ፣ ከዘርፉ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ከመንግሥት ጋር በመሆን በዘላቂነት መፍታት ላይ በትጋት ይሠራል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አበባየሁ ግርማ፤የምክር ቤቱ አመራሮች ምርጫ ዲሞክራሲያዊነቱን ጠብቆ የተካሄደና ስኬታማ መሆኑን አንስተዋል። ምክር ቤቱ በተለይ በከፍተኛ አምራቾች በአነስትኛ ኢንዱስትሪዎች መካከል የልምድና የቴክኖሎጂ ልውውጥን በማስፋት ረገድ በትኩረት እንዲሠራ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 80 ዓመታት የዕድገትና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ ቀጥሏል
Apr 8, 2026 105
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 80 ዓመታት የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለፁ። አየር መንገዱ ፈተናዎች በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡንም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የአየር መንገዱ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው፤ ተቋሙ ባለፋት ስምንት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያ የዕድገት፣ የትርፋማነት እና የሀገር ኩራት ምሳሌ ሆኖ መዝለቁን ገልጸዋል። አየር መንገዱ የመጀመሪያ በረራውን መጋቢት 30 ቀን 1938 ዓ.ም ማድረጉን ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በነበሩት ዓመታት ባስመዘገበው ተከታታይ ዕድገት በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ 145 መዳረሻዎች ያሉት ግዙፍ አየር መንገድ ለመሆን መብቃቱን ተናግረዋል። አየር መንገዱ ዘመኑ ያፈራቸውን እጅግ ዘመናዊ አውሮፕላኖች በመጠቀም ለደንበኞቹ የላቀ አገልግሎት እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቅሰው፥ በተለይም በተቋም ግንባታ ረገድ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት የራሱን አውሮፕላኖች ጥገና ማከናወን የሚያስችል ሙሉ አቅም የፈጠረ ሲሆን ይህም ለኩባንያው ዘላቂ ዕድገት ትልቅ መሠረት መጣሉን አመላክተዋል። የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ለማፍራት የራሱ አቪዬሽን አካዳሚ ያለው አየር መንገዱ፥ የአፍሪካ ትልቁን የአቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በመገንባት በታሪኩ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው ስኬት ማስመዝገቡን ገልጸዋል። አየር መንገዱ ራዕዩን መሸከም የሚችል ብቁ የሰው ኃይል ማፍራት እና የሥራ ሥነ-ምግባር ያለው ታታሪ ሠራተኛ በመፍጠር ረገድ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል። የካርጎ የጭነት አገልግሎት አቅሙን ከማሳደጉም በላይ በርካታ ደጋፊ መሠረተ ልማቶችን ገንብቷል ብለዋል። እነዚህ የተቀናጁ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችና የደንበኞችን እርካታ ታሳቢ ያደረጉ አሰራሮች አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የገበያ ውድድር ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥልና አስተማማኝ ዕድገት እንዲያስመዘግብ አስችለውታል ነው ያሉት። አየር መንገዱ 150 አውሮፕላኖች ያሉት ሲሆን የበረራ ተደራሽነቱንና ጥራቱን ይበልጥ ለማሳደግ 117 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለመግዛት በሂደት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። ያለፉት ሰማንያ ዓመታት ለአየር መንገዱ የታታሪነት፣ የጠንክሮ መስራት እና የስኬት ዘመናት መሆናቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገጠሙትን ፈተናዎች በጽናት በማለፍ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም መሆኑን በተግባር ማረጋገጡን ጠቅሰዋል።
በዓላትን ስናከብር የተቸገሩትን በማሰብና ካለን ላይ በማካፈል ሊሆን ይገባል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Apr 8, 2026 88
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በዓላትን ስናከብር የተቸገሩትን በማሰብና ካለን ላይ በማካፈል ሊሆን እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ መጪው የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው እና አቅመ ደካሞች የህብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ አጋርተዋል። ከንቲባዋ በማዕድ ማጋራት መርሃግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በዓላትን ስናከብር የተቸገሩትን በማሰብና ካለን ላይ በማካፈል ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። ከተማ አስተዳደሩ ይህንን ተግባር በየዓመቱ የሚያከናውነው ዜጎች በዓላትን በደስታ እንዲያሳልፉ ለማስቻል መሆኑን ተናግረዋል። አቅመ ደካሞችንና አረጋውያንን በመደገፍ በዓልን በጋራ ማክበር የቆየው የኢትዮጵያውያን መልካም እሴት መሆኑን አንስተው፤ የከተማ አስተዳደሩ ይህንኑ በጎ ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ከንቲባዋ ይህ ድጋፍ እንዲደረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ ባለሀብቶችና ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይመር ከበደ በበኩላቸው፤ በከተማ አስተዳደሩ በሰው ተኮር ስራዎች የመረዳዳት የመደጋገፍ ባህል እያሳደግን እንገኛለን ብለዋል። በዛሬው መርሃግብር ከ233 ሺህ በላይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ነዋሪዎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የዲጅታል ልማት ስትራቴጂ ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት ነው
Apr 8, 2026 86
መቀሌ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የዲጅታል ልማት ስትራቴጂ ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትግበራ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በቀጣይ አምስት ዓመታት የሚከናወን ቀጣይነት ያለው ስትራቴጂክ ፕላን ይፋ በማድረግ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል። የ2025 ስትራቴጂክ ተግበራ ስኬት ተደርገው ከሚወሰዱት መካከል የባንኮች የዲጅታል አገልግሎት መሳለጥ፣ የቴሌብር አገልግሎት፣ የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ፣ የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና እና ሌሎችም ይገኙበታል። የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ፤ የአዳዲስ ፈጠራዎች፣ የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ በዲጅታል የታገዙ መሆናቸውም ለዘርፉ እድገትና ማንሰራራት ማሳያዎች መሆናቸውን መግለጽ ይቻላል። ከዚህ ስኬትም በመነሳት የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ይፋ ተደርጎ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ይገኛል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ በትግራይ ክልል ያነጋገራቸው የዘርፉ ባለሙያዎች በዲጅታል ልማት ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራት አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከባለሙያዎቹ መካከል ሰሎሞን ፀጋይ፤ በተለይም የቴሌብር አገልግሎት፣ የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ፣ የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና ለዘርፉ መሰረት ያኖሩ መሆናቸውን አስረድተዋል። የተቋማት የዲጅታል አገልግሎት እየተስፋፋ መምጣት ሌላኛው ስኬት መሆኑንም ጠቅሰዋል። ከዚህ ስኬት በመነሳትም በቀጣይ አምስት አመታት የሚተገበረው ስትራቴጂክ እቅድ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑን ገልጸዋል። የድጅታል ቴክኖሎጂ ምርምርና ጥናት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሰሎሞን ገብረመድህን በበኩላቸው በተለይም ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው ለዘርፉ ልማትና አድገት ትልቅ አቅም መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እቅድን ለማሳከት ስልጠናዎች እንዳሉ ሆነው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የዘርፉ ባለሙያዎች በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ሌላኛው የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሀጎስ ገብረፃድቅ፤ በዲጅታል ቴክኖሎጂ እንደ ሀገር የተከናወኑ ተግባራትና በቀጣይ የተያዙ እቅዶች የሚያጓጉ መሆኑን ገልጸዋል። በገጠርና በከተሞች የዲጅታል አገልገግሎትን በማስፋት ዜጎች ፈጣን፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ መትጋት ይጠበቅብናል ብለዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከልም የዲጅታል ትግበራ የማይተካ ሚና የሚኖረው መሆኑን አስረድተዋል።
የአርማወር ሐንሰን ምርምር ኢንስቲትዩት ችግር ፈቺ የምርምርና ፈጠራ ውጤቶችን እያበረከተ ነው
Apr 7, 2026 190
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በሳይንሳዊ ምርምርና በፈጠራ ሥራዎች በሀገርና በአህጉር ደረጃ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጡ ውጤቶችን እያስመዘገበ መሆኑን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም የተገነባውንና ዘመናዊ መሠረተ ልማቶችን የያዘውን የምርምር ማዕከል መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መርቀው ከፍተዋል። በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክትም ማዕከሉ ኢትዮጵያና አፍሪካ በሳይንሱ ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲሸጋገሩ ትልቅ መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል። ይህ ዘመናዊ የምርምር ማዕከል ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ በመድሃኒትና በክትባት ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ሥፍራ መሆኑን ተናግረዋል። የአርማወር ሐንሰን ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በከፍተኛ አቅምና በውጤታማነት እየሠራ ነው። ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለይም እንደ ሳንባ ነቀርሳ (ቲቢ)፣ ወባ፣ ሚኒንጃይትስና ኒሞኒያ ባሉ ተላላፊ በሽታዎች ላይ ውጤታማ ጥናቶችን ማድረጉን ጠቅሰዋል። ለአብነትም የሳንባ ነቀርሳ ሕክምና ጊዜን ለማሳጠር የተደረገው ምርምር ለሕዝቡ የጤና ችግር ቀጥተኛ መፍትሔ የሚሰጥ ነው ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ በዓለም አቀፍ የሳይንስ መድረክ ላይ የኢትዮጵያን አሻራ በጉልህ እያሳረፈ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በየዓመቱ ከ80 እስከ 100 የሚደርሱ የምርምር ሥራዎች በታዋቂ የሳይንስ መጽሔቶች ላይ እንዲታተሙ በማድረግ ኢትዮጵያንና አፍሪካን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በስፋት እያስተዋወቀ ነውም ብለዋል። የተጠናቀቁና ውጤታማነታቸው የተረጋገጠ ምርምሮችም በቅርቡ ለሕዝብ ይፋ እንደሚሆኑ ፕሮፌሰር አፈወርቅ አረጋግጠዋል። ትኩረቱን ይበልጥ በማስፋት ከተላላፊ በሽታዎች በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት በስፋት እየታዩ ባሉ ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ላይ ጥናቶችን እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ ከጤና ዘርፍ ባለፈ ከሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የተለያዩ የሕክምና መሣሪያዎችን በማምረት ላይ እንደሚገኝም አንስተዋል።
ዩኒቨርሲቲው የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቷል
Apr 4, 2026 291
ወላይታ ሶዶ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። በዩኒቨርሲቲው "የአፈር ለምነትንና ጤናማነትን ማስጠበቅ ለግብርና ሽግግር" በሚል መሪ ሃሳብ 14ኛው ዙር ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ተካሂዷል። በወቅቱ በዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አክበር ጩፎ(ዶ/ር) እንደገለፁት፤ ዩኒቨርሲቲው የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል። የአፈር ለምነትና ጤናማነትን መጠበቅ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድግ በመሆኑ ለግብርና ዘርፍ ምርምሮች ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን በዘርፉ የተሰማሩ ተመራማሪዎችን በመደገፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በበጀት ዓመቱ ከ79 ሚሊየን ብር በላይ በጀት በመመደብ ከ50 በላይ የምርምር፣ 54 የማህበረሰብ ተኮር እንዲሁም ከ14 በላይ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን እየሰራ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ(ዶ/ር) ናቸው። በዩኒቨርሲቲው ያለውን ዕውቀት ከሀብት ጋር ለማቀናጀት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ስለመሆኑም ገልጸዋል። በዚህም የዘንድሮው 14ኛው ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ የአፈር ጤንነትና ምርታማነት ላይ አተኩሮ መዘጋጀቱን ጠቁመው በዘርፉ የተሰማሩ ምሁራንና ባለሙያዎች ቅንጅታቸውን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል አበክረው መስራት እንዳለባቸውም አመልክተዋል። በዩኒቨርሲቲው የአፈር ሳይንስ ጥናት ፕሮፌሰር ፋኑኤል ላዕከማርያም ፅሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት በአፈር ዙሪያ የሚደረጉ ምርምሮች ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር የሰው፣ የአካባቢ እና የእንስሳትን ጤና ለማስጠበቅ ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ። በጥናታዊ ጽሁፋቸው የአፈር እርጥበትን ማስጠበቅ፣ አሲዳማነትን መቀነስ፣ ምርታማነትን መጨመርና ካርቦንን አምቆ የመያዝ አቅምን ማሳደግ ላይ ያተኮረ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም የተለያዩ ጥናቶች መስራታቸውን ጠቁመው ይህም መንግስት ዘርፉን ለማሻሻል የጀመረውን ውጥን የሚደግፍ በመሆኑ ወደ አርሶ አደሮች በማምጣት እንደሚተገበርም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የተፈጥሮ ሀብት አያያዝና የአየር ንብረጥ ለውጥ መቋቋም ፕሮግራም ዳይሬክተር አወቀ ሙሉዓለም(ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋማቸው የሀገሪቱን ግብርና ለማሻገር በጥናት የተደገፈ ስራ በመስራት የግብርናን ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ መንግስት በዘርፉ የያዘውን ውጥን ለማሳካት እየተጋ መሆኑን በመጥቀስ ለስራው ውጤታማነት ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ይህም አርሶ አደሩ ከቤተሰብ ፍጆታ ያለፈ ትርፍ ምርት በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ገበያን በማረጋጋት በኩል አበርክቶ እንዲኖረው ትልቅ ድርሻ መወጣቱን አመልክተዋል። በመድረኩ ከ10 በላይ ጥናታዊ ጽሁፎች የቀረቡ ሲሆን ሙያዊ ውይይት ተደርጎ የፖሊሲ አቅጣጫ የማመላከት ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል።
በምርምር ስራዎች የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገው ጥረት ይጠናከራል
Apr 4, 2026 508
ሰመራ፣መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ) ፡-በምርምር ስራዎች የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት ማጠናከር እንደሚገባ የሠመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ዓሊ ተናገሩ። በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠነኛ ጊዜ የተዘጋጀ የአደጋ ተጋላጭ ማህበረሰብ ዝግጁነትና መቋቋም ላይ ያተኮረ ሲምፖዚየም በሰመራ ከተማ ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እንደተናገሩት፤ የምርምር ስራዎችን በማጠናከርና ተግባራዊ በማድረግ የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት መደገፍ ይገባል። የምርምር ውጤቶቹ ማህበረሰቡን ከማንቃትና ተጋላጭ እንዳይሆኑ ከማድረግ አኳያ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። በተለይም ተመራማሪዎች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት የአካባቢውን ችግር ተረድተው እገዛ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተው በአካባቢው የሚገነቡ ህንፃዎች ጭምር ግምት ውስጥ ሊገቡ እንደሚገባም አመልክተዋል። በሲምፖዚየሙ ላይ የተገኙት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመሬት መንቀጥቀጥ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አታላይ አየለ በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ አደጋዎች ከመከሰታቸው በፊት ዝግጅት ማድረጉ የጉዳት መጠኑን ለመቀነስ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ውሳኔ ሰጪ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ማድረግ፣ ፖሊሲዎችን ማጤንና የህንፃ ግንባታ ደረጃ ግልፅ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። መገናኛ ብዙሃን ጉዳዩን አስመልክተው እያከናወኑ ያለው የግንዛቤ ማስጨበጥ ተግባር ሊጠናከር እንደሚገባ ጠቁመው የምርምር ግኝቶችን በየጊዜው በማውጣት ለሚመለከታቸው አካላት ማጋራት ይገባል ብለዋል። በመድረኩም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተመራማሪዎች፣ የትምህርት ሚኒስቴርና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል
Apr 8, 2026 64
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከቀኑ 10 ሰዓት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ቅዱስ ጊዮርጊስ በሊጉ ካደረጋቸው 24 ጨዋታዎች መካከል ሰባቱን ሲያሸንፍ፤ በ10 ሽንፈት አስተናግዷል። በሰባት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በ24ቱ ጨዋታዎች ላይ 18 ጎሎችን ሲያስቆጥር 21 ጎሎች ተቆጥረውበታል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ28 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ተጋጣሚው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ 25 ጨዋታዎችን አድርጎ በዘጠኙ አሸንፎ በአምስቱ ተሸንፎ በቀሪ 11 ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 19 ግቦችን ሲያስቆጥር 13 ጎሎችን አስተናግዷል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ38 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። በ25ኛ ሳምንት ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 ያሸነፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ካሸነፈ ከወራጅ ቀጠና ይወጣል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ25ኛ ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ቡድኑ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይፋለማል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ቡና ከሸገር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮጵያ ቡና እስከ አሁን በሊጉ 24 ጨዋታዎችን አድርጎ 10 ጊዜ ሲያሸንፍ፤ በዘጠኙ ተሸንፏል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 24 ግቦችን ሲያስቆጥር በተመሳሳይ 24 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ35 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሸገር ከተማ በበኩሉ በሊጉ ባከናወናቸው 25 ጨዋታዎች በስድስቱ ሲያሸንፍ ሰባት ጊዜ ሽንፈት አጋጥሞታል። በቀሪ 12 ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 22 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 23 ግቦች ተቆጥረውበታል። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በ30 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቡና ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ተጋጣሚው ሸገር ከተማ ድል ከቀናው በ25ኛ ሳምንት በአርባምንጭ ከተማ ካስተናገደው የ2 ለ 1 ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ይመለሳል። ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመቀሌ 70 እንደርታ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። የ2016 ዓ.ም የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ30 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። መቀሌ 70 እንደርታ በ23 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በ25ኛ ሳምንት ከወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ የተለያየው ንግድ ባንክ ማሸነፍ ወደ ድል መንገድ ይመልሰዋል። ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ያላሸነፈው መቀሌ 70 እንደርታ ጨዋታው ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት በሚያደርገው ትግል ወሳኝ የሚባል ነው። ምድረ ገነት ሽሬ ከድሬዳዋ ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ባለፉት አራት ጨዋታዎች ከድል የራቀው ምድረ ገነት ሽሬ በ28 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ይገኛል። ድሬዳዋ ከተማ በ29 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት የሊጉ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ሲዳማ ቡና በ48 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና በ11 ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ይገኛል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ አዲስ ግደይ በ10 ጎሎች ይከተላል።
የኢትዮጵያ ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዩራጓይ ጋር ይጫወታል
Apr 8, 2026 107
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ያዘጋጀው የ"UEFA Frendship Cup" ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ውድድር በቱርክዬ ከመጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እየተካሄደ ይገኛል። በዚህ ውድድር ላይ ከተለያዩ አህጉራት የተውጣጡ ሀገራት የሚሳተፉ ሲሆን፤ የኢትየጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ጋር በፈጠረው ግንኙነት ከአፍሪካ ከሚሳተፉ ሁለት ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ መሆን ችላለች። በዚህም የኢትዮጵያ ከ18 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ይሳተፋል። በአሰልጣኝ ለሜቻ ግርማ የሚመራው ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ቀን 5 ሰዓት ከ30 ላይ ከዩራጓይ ጋር የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደርጋል። አሰልጣኝ ለሜቻ ለ22 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ ቡድኑ በአዲስ አበባ ዝግጅቱን ሲያደርግ የቆየ ሲሆን፤ ከትናንት በስቲያ ቱርክዬ ደርሷል። ብሔራዊ ቡድኑ ከጨዋታው በፊት በቱርክዬ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የልምምድ ሜዳ ልምምዱን አከናውኗል። በ"UEFA Frendship Cup" ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ውድድርላይ አስተናጋጇ ቱርክዬን ጨምሮ ኢትዮጵያ፣ ኖርዌይ፣ ኡዝቤኪስታን፣ ኮስታሪካ፣ ፓራጓይ፣ ዩራጓይ እና ሞሮኮ ተሳታፊ ናቸው። ኢትዮጵያ ከዩራጓይ በተጨማሪ ከኖርዌይ እና ኮስታሪካ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች። የወዳጅነት ስፖርታዊ ሁነቱ ከውድድር ባለፈ በአህጉራት መካከል ያለውን የእግር ኳስ ልማት ትብብርን ማጠናከር እና የልምድ ልውውጥ ማድረግን ያለመ ነው። በተጨማሪም የታዳጊ ሴት እግር ኳስ ተጫዋቾች ምልመላ የሚደረግ ሲሆን፤ ይህም ለኢትዮጵያ ተጫዋቾች መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። የ"UEFA Frendship Cup" ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ውድድር እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል
Apr 8, 2026 64
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30 /2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከቀኑ 10 ሰዓት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ቅዱስ ጊዮርጊስ በሊጉ ባደረጋቸው 24 ጨዋታዎች መካከል ሰባቱን ሲያሸንፍ በ10ሩ ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በሰባት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በ24ቱ ጨዋታዎች ላይ 18 ጎሎችን ሲያስቆጥር 21 ጎሎች ተቆጥረውበታል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ28 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ተጋጣሚው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ 25 ጨዋታዎችን አድርጎ በዘጠኙ አሸንፎ በአምስቱ ተሸንፎ በቀሪ 11 ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 19 ግቦችን ሲያስቆጥር 13 ጎሎችን አስተናግዷል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ38 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። በ25ኛ ሳምንት ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 ያሸነፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ካሸነፈ ከወራጅ ቀጠና ይወጣል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ25ኛ ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ቡድኑ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይፋለማል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ቡና ከሸገር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮጵያ ቡና እስከ አሁን በሊጉ 24 ጨዋታዎችን አድርጎ 10 ጊዜ ሲያሸንፍ በዘጠኙ ተሸንፏል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 24 ግቦችን ሲያስቆጥር በተመሳሳይ 24 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ35 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሸገር ከተማ በበኩሉ በሊጉ ባከናወናቸው 25 ጨዋታዎች በስድስቱ ሲያሸንፍ ሰባት ጊዜ ሽንፈት አጋጥሞታል። በቀሪ 12 ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 22 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 23 ግቦች ተቆጥረውበታል። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በ30 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቡና ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ተጋጣሚው ሸገር ከተማ ድል ቀናው በ25ኛ ሳምንት በአርባምንጭ ከተማ ካስተናገደው የ2 ለ 1 ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ይመለሳል። ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመቀሌ 70 እንደርታ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። የ2016 ዓ.ም የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ30 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። መቀሌ 70 እንደርታ በ23 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በ25ኛ ሳምንት ከወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ የተለያየው ንግድ ባንክ ማሸነፍ ወደ ድል መንገድ ይመልሰዋል። ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ያላሸነፈው መቀሌ 70 እንደርታ ጨዋታው ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት በሚያደርገው ትግል ወሳኝ የሚባል ነው። ምድረ ገነት ሽሬ ከድሬዳዋ ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ባለፉት አራት ጨዋታዎች ከድል የራቀው ምድረ ገነት ሽሬ በ28 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ይገኛል። ድሬዳዋ ከተማ በ29 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት የሊጉ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት እስከ ሚያዚያ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ሲዳማ ቡና በ48 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና በ11 ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ይገኛል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ አዲስ ግደይ በ10 ጎሎች ይከተላል።
በሻምፒዮንስ ሊጉ ፒኤስጂ ከሊቨርፑል ባርሴሎና ከአትሌቲኮ ማድሪድ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ተጠባቂ ናቸው
Apr 8, 2026 91
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018(ኢዜአ):- በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ሁለት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ምሽት አራት ሰዓት ላይ ፒኤስጂ ሊቨርፑልን በፓርክ ደ ፕሪንስ ያስተናግዳል። የፈረንሳዩ ፒኤስጂ በጥሎ ማለፉ ቼልሲን በማሸነፍ ስምንት ውስጥ ገብቷል። ተጋጣሚው ሊቨርፑል ጋላታሳራይን በመርታት ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ሁለቱ ቡድኖች በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሲገናኙ የአሁኑ ለአምስተኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም እርስ በእርስ ባደረጓቸው አራት ጨዋታዎች ሁለቱም ቡድኖች በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ አሸንፈዋል። ቡድኖቹ በአራቱ ጨዋታዎች ላይ በተመሳሳይ አምስት ግቦችን አስቆጥረዋል። እ.አ.አ 2024/25 በጥሎ ማለፉ ተገናኝተው ፒኤስጂ በድምር ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜ መግባቱ የሚታወስ ነው። የፓሪሱ ክለብ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ነው። ሊቨርፑል የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ስድስት ጊዜ አንስቷል። ጨዋታው ለተመልካች ሳቢ እና ተመጣጣኝ ፉክክር ይደረግበታል። ሌላኛው ጨዋታ ምሽት አራት ሰዓት ላይ ባርሴሎና እና አትሌቲኮ ማድሪድን በካምፕ ኑ ስታዲየም ያገናኛል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ ሩብ ፍጻሜ የገቡት የእንግሊዝ ክለቦችን በመርታት ነው። ባርሴሎና ኒውካስትል ዩናይትድን፣ አትሌቲኮ ማድሪድ ቶተንሃም ሆትስፐርስን አሸንፈዋል። ቡድኖቹ በሻምፒዮንስ ሊጉ ለአምስተኛ ጊዜ ይገናኛሉ። ከዚህ በፊት ባደረጓቸው አራት ጨዋታዎች አትሌቲኮ ማድሪድን ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ ባርሴሎና አንድ ጊዜ ድል ቀንቶታል። በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። በአራቱ ጨዋታዎች ላይ አትሌቲኮ ማድሪድ አምስት ግቦችን ሲያስቆጥር ባርሴሎና ሶስት ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሁለቱ ቡድኖች ለመጨረሻ ጊዜ በውድድሩ ላይ የተገናኙት እ.አ.አ 2015/16 ነበር። በወቅቱ በሩብ ፍጻሜ ተገናኝተው አትሌቲኮ ማድሪድ በድምር ውጤት 3 ለ 2 በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜ ማለፉ አይዘነጋም። ከ10 ዓመታት በኋላ በድጋሚ በሩብ ፍጻሜው ተገናኝተዋል። ጨዋታው ጠንካራ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ ከካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ የደን አያያዝ ስራዎችን እያከናወነች ነው
Apr 4, 2026 185
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ ዘላቂ የመሬትና የደን አስተዳደር ልምዶችን እያሳደገች መሆኑን የአረንጓዴ አሻራ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) ገለጹ። ዶክተር አደፍርስ ወርቁ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የካርበን ክምችት መኖሩን በማንሳት፤ አብላጫው በደን ሀብት ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ ሀገሪቱ ከካርበን ሽያጭ የምታገኘው ገቢ እንዲጨምር የጎላ ሚና እየተጫዎተ እንዳለ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ የብዝሃ ህይወት ባለቤት በመሆኗ የተሻለ የካርበን ክምችት ለመያዝ የሚያስችል ተስማሚ ሥነ-ምህዳር እንዳላት ዶክተር አደፍርስ ገልጸዋል። ሀገሪቱ በአየር ንብረትና በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈች መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ካርበንን ከአየር ላይ በማስወገድ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ መንገድ እንዲከማች እያደረገ ነው ብለዋል። ቀደም ሲል በደን መመንጠርና ባልተገባ የመሬት አያያዝ ምክንያት ወደ ህዋ ይለቀቅ የነበረውን ሙቀት አማቂ ጋዝ መከላከል የሚያስችሉ ተግባራት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካይነት እየተተገበሩ እንዳለ አስረድተዋል። በዚህም ከካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ ዘላቂ የመሬት እና የደን አሥተዳደር ልምዶችን ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልጸዋል። ሁለተኛው ደግሞ እጽዋት በሚተከሉበት ወቅት ቀደም ሲል ወደ ህዋ የሄደውን ካርበን አምቀው የሚመልሱበትን አሰራር ተግባራዊ በማድረግ እና ከልቀት የተጠበቀውን ካርበን ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እያከናወነች ባለችው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት የካርበን ሽያጭን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑንና ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር የግዢ ውል ስምምነት እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የኖርዌይ መንግስት እንደመነሻ የ75 ሚሊዮን ዶላር የካርበን ግዢ እንዲሁም የዓለም ባንክም እንዲሁ የግዢ ውል ማሰሩን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ኖርዌይ እና የዓለም ባንክ ሊገዙት ከሚፈልጉት በላይ ካርበን ማመንጨቷን ጠቁመው፤ እስከ አንድ ቢሊየን ዶላር ሊያመጣ የሚችል ካርበን ሀብት መኖሩን ገልጸዋል። በዓለም ገበያ ላይ ለካርበን ግዢ የሚመደበውን ከፍተኛ ሀብት ወደ ኢትዮጵያ የካርበን ሽያጭ ማምጣት የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። በዓለም ላይ ያለውን የካርበን ፋይናንስ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከማጠናከር ባለፈ ሰነዶች የማደራጀትና ሌሎች ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ለዲጂታልና ታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ ነው
Apr 3, 2026 418
አዳማ ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎትን ከማስፋት ባሻገር ለዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ ቴሌኮም በአዳማ ከተማ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከል በመገንባት በዛሬው እለት አገልግሎት አስጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ በኢትዮጵያ የዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአዳማ ከተማ ተገንብቶ በዛሬው እለት ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከልም የዚሁ ልማት ጥረት አካል መሆኑን ጠቁመዋል። የአዳማው ማእከል በአንድ ጊዜ 12 ተሽከርካሪዎችን ቻርጅ የሚያደርግ አቅም እንዳለው ተናግረው በሌሎች አካባቢዎችም የማስፋት እቅድ መኖሩን ገልጸዋል። ኢትዮ ቴሌኮም ከፈጣንና ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎት በተጨማሪ ለዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም መሰረት አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ከተሞች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጀ ማድረጊያ ማዕከላትን በማስፋፋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ፤ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት ተቀርፆ አሰራርና አገልግሎቶችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ሂደት የኢትዮ ቴሌኮም አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አንስተው በከተማዋ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከል ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል።
በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኞቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ይኖራል
Apr 3, 2026 120
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኞቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጠንና ሥርጭት የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፤ ከመጋቢት 23 እስከ ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም የበልግ ዝናብ በመጠንና ስርጭት ከፍተኛ ድርሻ የሚወስድበት ወቅት መሆኑን ገልጿል። በዚህም በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኛዎቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ከቀደሙት ሁለት የበልግ ወራት በመጠንና ሥርጭት የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ እንደሚኖር አስታውቋል። ይህም የአየር ጠባይ ሁኔታ የበልግ አብቃይና ተጠቃሚ አካባቢዎች ለሚያከናውኑት የግብርና ሥራ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር ይጠበቃል ብሏል ኢንስቲትዩቱ በመግለጫው። በተለይም በተያዘው የመጋቢት ወር የሚስተዋለው ተከታታይ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ በቡቃያና በተለያየ የዕድገት ደረጃ ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎች ምርታማነት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጿል። በደቡብና ደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ የሚጠበቀው እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ለቦረና፣ ጉጂና መሰል ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች ሰብል ልማት፣ ግጦሽ መሬትና የውሃ አቅርቦት ወሳኝ መሆኑንም አመላክቷል። በዚህም የበልግ አብቃይ አካባቢ አርሶና አርብቶ አደሮች ማሳቸውን በማዘጋጀት የሚጠበቀውን አመቺ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ለመጠቀም ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ አሳስቧል። በበልግ ዝናብ መዋዠቅ አዝማሚያ ምክንያት ዝናብ አጠር የሆኑ አካባቢዎች የሚያጋጥማቸውን ተከታታይ ደረቃማ ሁኔታ ለመቋቋም እርጥበትን በማሳ ማቆየት የሚያስችል ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ኢንስቲትዩቱ አስውገንዝቧል። በሌላ በኩል በአንዳንድ አካባቢዎች በሚኖር ከባድ ዝናብ ሊፈጠር ከሚችል የመሬት መንሸራተት፣ የአፈር መሸርሸርና ቅፅበታዊ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭነት ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስቧል።
የክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዜጎችን ተጠቃሚነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው
Apr 3, 2026 124
ባህር ዳር፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በለውጡ ዓመታት የተተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዜጎችን ተጠቃሚነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከእለት ወደ እለት ስኬታማ እየሆነ መምጣቱ እየተመሰከረለት ነው። በመርሃ ግብሩ በብዛትና እና በአይነት መጠነ ሰፊ ችግኞች ተከላ መካሄዱን ለአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፤ ለደን ሽፋን መጨመር ብሎም የምግብ ዋስትን ለማረጋገጥ እያስቻለ ነው። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ መሰሉ ብርሃኑ ለኢዜአ እንዳሉት፤በለውጡ ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዘርፉን ልማት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው። መርሃ ግብሩ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ለውጥ መሻሻል፤ ለደን ሽፋን መጨመር እና የምግብ ዋስትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ መሆኑንም አስረድተዋል። መርሃ ግብሩ ተግባራዊ መደረጉ በክልሉ 13 ነጥብ 9 በመቶ የነበረውን የደን ሽፋን ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ለማስደግ እንደተቻለም ነው የተናገሩት። በነዚሁ የለውጥ አመታት በ22 ሺህ 189 ተፋሰሶች ላይ በተካሔደው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ምርታማነት ለማሳደግ ያስቻለ መሆኑንም አብራርተዋል። የአረንጓደ ልማቱ በተለይም ለንብ ማነብ፣ ለእንስሳት እርባታና ለፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አንስተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 329
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 261
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 563
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው
Mar 22, 2026 253
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
የጤና ነገር ...
Apr 3, 2026 2078
በዮሐንስ ደርበው የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። የኒውትሬሽን ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ የሰው ልጅ የሰውነት ክፍል 60 በመቶው ውኃ እንደመሆኑ ለተስተካከለ ጤና ሚዛን መጠበቅ በቂ ውኃ መጠጣት ይገባል። ውኃን በትክክለኛው መጠንና ጊዜ መውሰድ ከተቻለ የኩላሊት ህመም ተጋላጭነትን 50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ነገር ግን ሰውነት የሚፈልገውን የውኃ መጠን በአግባቡ ካላገኘ ለዕለታዊ እና በጊዜ ሂደት ሥር ለሚሰድዱ ህመሞች የመጋለጥ ዕድል እንደሚጨምርም ያነሳሉ። ለመሆኑ ሰውነት የሚፈልገውና በቂ የውኃ መጠን የሚባለው መጠኑ ስንት ነው? በቂ ውኃ አለመጠጣትስ የሚያስከትለው ችግር ምንድን ነው? በሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎች ላይ የኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ምላሽ አላቸው። አንድ ሰው የሚያስፈልገው የውኃ መጠን በዕድሜ፣ ጾታ፣ በሥራ ባሕርይ፣ በመኖርያ አካባቢ፣ እንደ ጤና ሁኔታው እና እንደ ሰውነት ክብደቱ እንደሚወሰንም በምላሻቸው አስገንዝበዋል። ለምሳሌ የስኳር ታማሚዎች፣ የምታጠባ እናት፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎች፣ ብዙ አድካሚና ላብ የሚያወጡ፣ በሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በቀን 3 ሊትር ውኃ መጠጣት አለባቸው ይላሉ። በአማካይ ግን በቀን አንድ ሰው ከ2 እስከ 3 ሊትር ውኃ መጠጣት እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። ጤናማ ሕይወት የሚመሠረተው ከውኃ ነው፤ ለምሳሌ ውኃማውን 60 በመቶ የሰውነት ክፍል ሚዛን ለማስጠበቅ የግድ አስፈላጊውን መጠን ውኃ መጠጣት እንደሚገባ ይመክራሉ። በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው ሕይወታዊ ሂደት (ባዮሎጂካል ፕሮሰስ) ውኃን መሠረት ያደረገ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ለተስተካከለ የሥርዓተ-ምግብ ሂደት፣ ቆሻሻን ከሰውነት አጣርቶ ለማስወጣት፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ሥራን ለማስተካከል እና ለሌሎችም በርካታ የሰውነት ክፍሎች የተሳለጠ ተግባር ውኃ ቁልፍ መሆኑን አንስተዋል። ይህን ተከትሎም ውኃ ካሎሪ አልባው መድኃኒት (ተፈጥሯዊው መድኃኒት) እስከመባል መድረሱን ነው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ያስረዱት። ሰውነት የሚያስፈልገውን ያህል ውኃ አለመጠጣት ግን ድካም ያስከትላል፤ ለማየት፣ ለመንቀሳቀስ፣ ለመሥራት፣ ለማሰብ፣ ለመረጋጋት . . . አያስችልምና ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንድ ሰው ውኃ የመጠማት መጠኑ ከአራት በመቶ በላይ ከሆነ ለሞት ሊጋለጥ እንደሚችልም ጠቅሰዋል። ውኃ አለመጠጣት፤ የጨጓራ ህመምን በማባባስ ማስገሳት፣ የቆዳ ድርቀትና ግርጣት፣ የኩላሊት ህመም ሌሎች የሰውነት ክፍሎችም ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ያደርጋል ነው ያሉት። ከምግብ በፊት 30 ደቂቃ ቀድሞ ውኃ መጠጣት ውፍረትን ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በቂ ውኃ ከመጠጣት በተጨማሪ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን ማዘውተር እንደሚመከርም ገልጸዋል። የፈላ ውኃ እና የዝናብ ውኃን በብዛት መጠጣት በሰውነት ውስጥ ያሉ ንጥረ ነገሮችን በማስወገድና በኩላሊት ላይም ጫና እንደሚፈጥር አመላክተዋል። ለተስተካከለ ጤናማ ሕይወት የግድ ውኃ መጠጣትን ልማድ ማድረግ እንደሚገባም ይመክራሉ። #ውኃ_መጠጣት #ጤና #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency
ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች
Apr 3, 2026 2172
በዮሐንስ ደርበው የለውጡ መንግሥት ኢትዮጵያን ማሥተዳደር ከጀመረ እነሆ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ላይ 8 ዓመት ሞላው። በእነዚህ ዓመታት በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊ ዘርፉ በዲፕሎማሲውና በሌሎችም መስኮች የተለያዩ ስኬቶች ተከናውነዋል። በእነዚህ ጥቂት ዓመታትም ለማሳካት ቀርቶ ለማሳብ የማይደፈሩ ብዙ ውጤቶችም ተመዝግበዋል። የተገኙት ስኬቶች ከጊዜያቸው የፈጠኑ ናቸው። ለዚህም ሕዝቡ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በነቂስ እየወጣ አድናቆቱን ገልጿል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰጡት የሰላ አመራርነትና ቁርጠኝነትም አክብሮቱንና ምሥጋናውን ገልጿል። የለውጡ መንግሥት አካሄድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የልማት ፕሮጀክቶችም በይበልጥ ተስፋፍተውና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መንግሥት ለሚያደርገው ጥረት ከጎኑ እንደሚቆሙም በድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተጋቧቸው መልዕክቶቻቸው አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ በለውጡ መንግሥት ለማሳካት ቀርቶ ለማሰብ የማይደፈሩ ተግባራት ተከናውነዋል። ከእነዚህ ከፍተኛ ጥቅም ከተገኘባቸው የታሪክ እጥፋትን ካሠረጹ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል ጥቂቶቹን ቀጥለን በወፍ በረር እንዳሥሣለን። ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። • የኮሪደር ልማት እንደምናውቀው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነትና ልዩ ትኩረት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከሁሉም አስቀድሞ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። አሁን ላይ ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የበርካታ ከተሞችን ገጽታ የቀየሩ አስደማሚ ሥራዎች ተከናውነውበታል። ይህም በገጠር ጭምር ተጠናክሮ የቀጠለ ጉዳይ ነው። ለዘመናት አሮጌ ገጽታዋን ይዛ ያሸለበችውን አዲስ አበባ እንደ አዲስ የፈጠራትም ይኸው ፕሮጀክት ነው። አሁን ላይ መዲናይቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን ለውጥ ዐይተው ዝም ማለት አልቻሉም። ከመደመማቸው አንጻር የዘወትር አጀንዳቸውም እያደረጓት ይገኛሉ። ይህንን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፤ ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ነው ማለታቸው ይታወሳል። ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑንንም አስረድተዋል። ከለውጡ መንግሥት ዐበይት የትኩረት መስኮች አንዱ የሆነውን የቱሪዝም ዘርፉን እንቅስቃሴ ለማሳደግም ቁልፍ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ድርብርብ ፕሮጀክት ነው የኮሪደር ልማት። • የበጋ መስኖ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የለውጡ መንግሥት ዋነኛ ትኩረቱ ነው። ለዚህም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አንዱ ማሳኪያ ሥልት አድርጎ እየተጋ ይገኛል። የበጋ መስኖ ስንዴ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ማስገባት አቁማ መላክ እንድትጀምር ያስቻለ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችና በሜካናይዜሽን ታግዞ በስፋት እየተሠራበትም ይገኛል። ከለውጡ መንግሥት ወዲህ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ምክንያት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምርታማነት ማደግና የሥራ ዕድል በመፍጠር አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብም ከፍተኛ ውጤት ተገኝቶበታል። ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ ስንዴ ላይ ባሳየችው ትጋት፤ ፍጆታዋን በራሷ ዐቅም የሸፈነችው፣ ስንዴን ከውጭ ማስገባትን ያቆመችው፤ ስንዴን ወደ ውጭ መላክ የጀመረችው በለውጡ መንግሥት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ በመሸለም ለጥረታቸው ዕውቅና መስጠቱም ይታወሳል። • መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይን ለማስፈጸም እዚያም እዚህም መንከራተት የግድ ነበር። በዚህ አያበቃምና ወረፋውም ሌላ ችግር ነው። መንግሥት በተለያዩ መድረኮች ባካሄዳቸው ሕዝባዊ ውይይቶች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉልን የሚሉ እሮሮዎች በረከቱ። መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል ሥራ ወደ ተግባር አሥገባ። በዚህም መሠረት ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ ጀመረ። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነውም አሉ። ለዚህ ቁርጠኝነታችን አንዱ ማሳያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመራቸውንም ገለጹ። እንግዲህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ ታግዘው በተሳለጠ ሂደት እንዲሰጡ በማድረግ የተገልጋይን እንግልት፣ ገንዘብ እና ጊዜ መቀነስ ያስቻለ አሠራር ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት ተደርጎም ይወሰዳል። በየከተሞቹም እየተስፋፋ ነው። • አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ አይ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ተጠቃሚ እንድትሆን ከፍተኛ ጉጉት እንዳላቸው በቁጭት በተለያዩ መድረኮች ያነሳሉ። ለዚህም መፍትሔ ዘይደው ተቋማትን ከማቋቋም ጀምሮ ለዘርፉ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ተግተዋል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂው ጋር አብሮ ለመጓዝ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን አቋቋመች። የኤ አይ ዩኒቨርሲቲ በመክፈት በግብርናው፣ በጤናው እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠርም በሂደት ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል። ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም አንስተዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ማለታቸው ይታወቃል። ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ ማስገንዘባቸውም ይታወሳል። • የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው። በዚህ ሂደት ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊታአውራሪነት ይጠቀሳል። በተደራጀና ተቋማዊ ሆኖ ባልተቆራረጠ አካሄድ እየተከናወነ ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተተከሉ ችግኞችም በየዘርፉ ተጠቃሚነት አድጓል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል። • የሌማት ትሩፋት ከመጋቢት ሥጦታዎች አንዱ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ነው። የምርት አቅርቦትን በማስፋት ለተረጋጋ ግብይት እና ለተመጣጠነ ሥርዓተ-ምግብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከት ላይም ይገኛል። ኢኒሼቲቩ ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለሀገራዊ የሥርዓተ-ምግብ መሻሻል ጉልኅ ሚና እየተጫወተ ነው። የዋጋ ንረትን በማረጋጋት፣ የምርት ስብጥርን በማሳደግና በዘላቂነት በማቅረብ ረገድም የጎላ ሚና አለው። የግድ ሰፋፊ መሬት መፈለግ ሳያሻ በትንሽ ቦታ ብዙ በማምረት ፍጆታን ከመሸፈን አልፎ ኢኮኖሚን በመደጎም እና የሥራ ዕድል በመፍጠርም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። • የቱሪስት መዳረሻ ልማት ቅርሶች እንዲጠገኑ፣ አዳዲስ ሎጂዎች እንዲገነቡ፣ በመዳረሻ ስፍራዎች መሠረተ-ልማት እንዲሟላ ያስቻሉ ተግባራት በለውጡ መንግሥት ተከናውነዋል፤ አሁንም ተጠናክሮ የቀጠለ እና ስኬታማ ኢኒሼቲቭ ነው። በዚህ ሂደት ከሐሳብ አመንጭነት ባሻገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የጻፉትን መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ ጭምር ለቅርስ ጥገናና ለቤተ-መጻሕፍት ግንባታ እንዲውል አድርገዋል። በተጨማሪም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት፤ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ ወደ ተግባር አስገብተዋል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። አማራጭ የቱሪስት መዳረሻም ሆነዋል። • የተቋማት ግንባታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል መሪል ሐሳብ በተካሄደው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ፤ የተቋማት ግንባታና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ብለዋል። በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ሲሉም አስገንዝበዋል በወቅቱ። ዘመን የማይለውጣቸው ዘላቂ ጠንካራ ሃገራዊ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ብዙ ርቀት መጓዝም ተችሏል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲሆኑ በማድረግ እና ሥርዓት በተለዋወጠ ቁጥር የማይፈርሱ ወይም የሚሻገሩ ተቋማት መገንባት ተችሏል። ይህ ትጋት ተጠናክሮም ቀጥሏል።
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3680
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … በኢዜአ ዐይን …! የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 437
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 4, 2026 1108
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 20 እስከ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ስለ አዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ አዲስ አበባ ከዋና ከተማ በላይ መሆኗን ገልጸው፤ በፈጣን እንቅስቃሴ ላይ ያለች፣ ወደ ኢትዮጵያ ነገ የመግቢያ በር፣ በፍጥነት እየተለወጠች ያለች የሀገር የልብ ትርታ፣ ሁሉንም አሳታፊ እና አርቆ አሳቢ የሆነ የከተማ ልማት ትልማችን መገለጫ ናት ብለዋል። ፈጣን መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት፣ የዘመናዊ ከተማ መፍትሔዎችን በማቅረብ፣ አካታች በሆነ መልኩ መኖሪያ ቤት በመገንባት እና ዘላቂ ዕድገትን በማረጋገጥ እየሠራን ያለነው ዛሬን ብቻ ሳይሆን ለነገው ትውልድ ጭምር ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ከተሞቻችን ሰዎችን ለማብቃት፣ ዐቅምን ለመጠቀም እና ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ ቅርጽ ይዘዋልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። • አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀው ከፍተዋል። በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው ብለዋል በወቅቱ። የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከል ማከተቱን አብራርተዋል። ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። • የአዲስ ስፖርት ፓርክ መመረቅ ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የከተማችንን እድሳት ለማፋጠን እና የዜጎቻችንን ክብር ለመመለስ የገባነውን ቃል አንዱ ማረጋገጫ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን በይፋ መርቀን ከፍተናል ብለዋል። በ5 ነጥብ 7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ፕሮጀክት፤ በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ 15 አትሌቶችን የሚዘክሩ የክብር ሐውልቶችን በፓርኩ መሃል በማቆም፣ የጀግኖቻችን ታሪክ ለተተኪ ትውልድ ስፖርተኞች ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋልም ነው ያሉት። የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስና የሜዳ ቴኒስ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የ800 ሜትር የሩጫ ትራክን ጨምሮ፤ እያንዳንዱ የዚህ ማዕከል ክፍል የዓለም አቀፍ መስፈርቶችን እንዲያሟላ ተደርጎ ተገንብቷል ሲሉም ገልፀዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በአፋር ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፋር ክልል ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት በአዋሽ ወንዝ ተፋሰስ በመሥኖ እየለማ ያለው የሱፍ ምርት ለተሻገረ ግብርና እና ለተሻገረ ገጠር ራዕያችን ተደማሪ ሃብት ነው ብለዋል። በአፋር ክልል ያየነው በመሥኖ ተፋሰስ በረሃ የመሰለውን ምድር የምርት መትረፍረፊያ የማድረግ ትጋት፤ ለሌሎች በተለይም ከዓመት እስከ ዓመት ዝናብ አጠር አካባቢዎች ትልቅ የመማሪያ ሠነድ እንደሚሆን አመላክተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በተካሄደው "የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ቅንጅት ለሀገራዊ ሰላም እና ደኅንነት" በሚል መሪ ሐሳብ በተካሄደው ብሔራዊ የደኅንነት ኮንፈረንስ ላይ የተሳተፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የጸጥታና ደኅንነት ተቋሞቻችን ችግርን ወደ ዕድል እንዲቀየሩ ያስቻሉ ናቸው ብለዋል፡፡ ጉዟችን ተጀመረ እንጂ አልተቋጨምና ከትናንት ዕዳዎች ተላቀን፣ የዛሬ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን ለነገው ትውልድ የምትመጥን ሀገር ለመገንባት በዓላማ ጽናት እንቀጥላለን ሲሉም አመላክተዋል። • ስለ መጋቢት 24 መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወደ ሥልጣን የመጣውን የለውጡን መንግሥት የሚደግፉ ሕዝባዊ ሰልፎች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ሰልፎች ላይም መንግሥት ባለፉት ሥምንት ዓመታት ያመጣቸውን ለውጦች እና የተገኙ ስኬቶችን የሚያወሱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) ለሰጡት ስኬታማ አመራርነት የሚያሞግሱና የሚያመሠግኑ መልዕክቶች ተስተጋብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ቀኑን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሕዝባዊ ግፊትና ትግል ያመጣው የመጋቢት ለውጥ ኢትዮጵያን ወደ ኋላ ያስቀሩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ስብራቶችን መጠገን ያስቻሉ ሪፎርሞች የተተገበሩበት ነው ብለዋል። ለሕዝባችን የላቀ ተጠቃሚነት፣ ለሀገራችን ክብርና ብልፅግና መሳካት አበክረን እንሠራለን ሲሉም ገልጸዋል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በበኩሉ ቀኑን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በኃይልና በምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ አስደማሚ ስኬቶችን አስመዝግባለች ብሏል። የለውጡን መሠረት ከማስፋትና ከማጽናት ወደ ማላቅ የተሸጋገረችው ኢትዮጵያ፤ በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌትነቷን በተግባር ታውጃለች ሲልም ገልጿል። ይህን ለውጥ ዕውን ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ፤ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በድል እንደሚያሳርጉት ጥርጥር የለውም ነው ያለው። • የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ስምምነት የኢትዮጵያ መንግሥት በInvest in Ethiopia 2026 ፎረም፤ ከቻይና፣ ፖላንድ፣ ሕንድ፣ ሲንጋፖር እና ኬንያ ከመጡ አጋሮች ጋር የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ታሪካዊ የኢንቨስትመንት ስምምነት መፈራረሙን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት አስታውቋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማዕድንና በአረንጓዴ አሞኒያ ዘርፎች ላይ ያተኮሩት እነዚህ ስምምነቶች፤ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ጉልህ ማሳያ ናቸው ብሏል። በተመሳሳይ ጽሕፈት ቤቱ ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለውን የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ የሚተካ የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 ሆኖ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል ብሏል። የ1954 የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየ በመሆኑ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት እና ከወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዘርፉ ካሉ አዳዲስ አሠራሮችና የቴክኖሎጂ እድገቶች አኳያ ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ መልኩ መከለሱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ባለፉት ዓመታት የአዲስ ሕግ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ብዙ ምክክር ተደርጎበት የጸደቀው የሕግ መድብል አዳዲስ አሠራሮችን የሚያስተዋውቅ፤ የወንጀል ምርመራ፣ ክስና ማስረጃ ሥርዓቱን ወደአዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው ሲልም አስገንዝቧል ጽሕፈት ቤቱ።
ባሳለፍነው ሳምንት
Mar 28, 2026 505
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 13 እስከ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • የ ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን እና የሰው ልጅ ታሪክ በጀመረበት ምድር የተገነባውን ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅት ሎጁ የዛሬ 50 እና 60 ዓመት መሠራት የነበረበት ቢሆንም፤ አሁን ስለዘገየን አንቆጭም ማለታቸው ይታወሳል። ይህን ስለሠራንም አንረካም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሩጫችን ገና ብዙ እንደሆነ፣ አፋር ገና እንዳልተነካ አስበን ይህን ጅማሮ ይበልጥ በማላቅ ለማስቀጠል እንተጋለን ሲሉም ተናግረዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከቃና ቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነም ገለጻ አድርገዋል። እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸውን ፋይዳም አንስተዋል። • ኢትዮጵያ በማላቦው ጉባዔ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ ወደ ማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ማላቦ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑዌል ኡሳ ኡዙዌን ጨምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጉባዔው ከመጋቢት 18 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ ሲሆን እስከ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቀጥላል። • የልማት ሥራዎች ጉብኝት በባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የባሕር ዳር ከተማን የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያጎሉና ግንባታቸው እየተፋጠኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ መሠረተ-ልማት እና የአየር መንገድ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገታችን የጎላ ፋይዳ ይኖራቸዋል ሲሉም በወቅቱ ገልጸዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጎንደርን የውኃ ጥም ይቆርጣል፤ የገበሬውን መሬት ያጠጣል፤ የአካባቢውን ምኅዳር ይለውጣል የተባለው የመገጭ የመጠጥ ውኃ ግድብ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተዋል። በዚሁ ወቅት የሀገር ሀብት ፈስሶባቸው መክነው እና ባክነው የቀሩ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ከሞት እያስነሡ ማፋጠን የዚህ መንግሥት ልዩ መለያው ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም የመገጭ ግድብ ምስክር መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ሳይና ሳቢያ የገጠር ቀበሌ የተገነቡ የገጠር ኮሪደር ሞዴል ቤቶችን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም በአንድ ወር የግንባታ ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀው ይህ ሞዴል መንደር በአካባቢው ለረጅም ዓመታት የቆየውን የጤና ጣቢያ፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎት ጥያቄ በተግባር መልሷል ብለዋል። በሀገራችን ከተማው ብቻ ሳይሆን ገጠሩም እኩል እየተዋበ፣ በልማት እየተገነባና በዕድገት ፍኖት ላይ በጽኑ መሠረት እየተራመደ ይገኛልም ነው ያሉት። ይህ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የማሸጋገር ትልቁ ማሳያችን ነው ሲሉም ገልጸዋል። • "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ በአዲስ አበባ 4ኛው "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም፤ የምንፈልገው ድጋፍን ሳይሆን አጋርነትን ነው፤ እርዳታን ሳይሆን ኢንቨስትመንትን ነው! ለባለ ሀብቶች ምቹ፣ ግልጽና ተራማጅ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ አዘጋጅተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ካፒታል፣ ለችሎታ እና ለዕድል በሯን ወለል አድርጋ መክፈቷንም አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ አሁን በፍጥነት ወደ ከፍታ እየገሠገሠች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ የዕድገት ጉዞ፤ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ባለ ሀብቶች ኢትዮጵያ ለእናንተ ዝግጁ የሆነ፣ በዕድሎችና በስኬቶች የተሞላ ታላቅ የኢንቨስትመንት መሶብ አላት፤ ኑ አብረን እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል! • የትግራይ ክልል አጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በሰጡት መግለጫም፤ ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ለመጀመርና ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል። በዚህም ከክልሉ ጊዜያዊ አሥተዳደር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀሌ እና በአዲስ አበባ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ጥረቶች ውስጥ ሂደቱን በክልሉ ለማካሄድ የሚያስችሉ አስቻይ ሁኔታዎች ባለመፈጠራቸው፤ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች ምርጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ እንዲከናወን መወሰኑንም አስረድተዋል።
ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት
Mar 26, 2026 215
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በኋላ የታዛቢነት (Observer) ደረጃን አገኝታለች። እ.ኤ.አ በ2006 የውጭ ንግድ ፖሊሲዋን የሚገልጽ ሰነድ ለድርጅቱ አቅርባለች። ሰነዱ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች፣ የወጪና ገቢ ንግድ ሕጎች፣ የቀረጥ፣ ከቀረጥ ውጭ ያሉ የንግድ ገደቦች፣ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ እና የኢንቨስትመንት ሕጎችን ያካተተ ነበር። በኢትዮጵያ እና በዓለም ንግድ ድርጅት መካከል የመጀመሪያው የድርድር ምዕራፍ የተጀመረው እ.አ.አ በ2008 ነው። ከእ.አ.አ 2008 እስከ 2012 በቆየው የቴክኒክ ድርድር ሶስት የስራ ቡድን ስብስባዎች ተካሂደዋል። በዚህ ወቅት የነበረው ድርድር በዋናነት ኢትዮጵያ ስለ ንግድ ሥርዓቷ ማብራሪያ የምትሰጥባቸው እንጂ፣ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘት አልቻሉም። ከእ.አ.አ 2012 እስከ 2019 የሁለቱ ወገኖች ድርድር ተቋርጦ ነበር፤ ለሰባት ዓመታት እንዲቋረጥ ያደረጉ የተለያዩ ምክንያቶች ይነሳሉ። በወቅቱ ስልጣን የነበረው የኢህአዴግ መንግስት "የገበያ ውድቀት" አለ ብሎ ያምን ነበር። ስለዚህም እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም እና ኢነርጂ ያሉ ስትራቴጂካዊ ዘርፎች በመንግስት እጅ መቆየት አለባቸው የሚል አቋም ነበረው። ይህ የመንግስት ጽንሰ ሀሳብ ድርጅቱ የተለያዩ ዘርፎች ለውጭ ክፍት መደረግ አለባቸው ከሚለው አቋም ጋር የሚጣጣም አልነበረም። በዓለም ንግድ ድርጅት የተጠየቁ የንግድ ስርዓትን የማዘመን ስራዎች በሚፈለገው መልኩ አለመሄዳቸውም ለድርድሩ መቆም እንደ ምክንያትነት ይነሳል። የለውጡ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ የአባልነት ድርድር በድጋሚ ነፍስ ዘርቷል። መንግስት በተለያዩ ዘርፎች የወሰዳቸው ጠንካራ የንግድ እና ኢኮኖሚ እርምጃዎች ድርድሩ በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀጥል አድርጓታል። መንግስት እንደ ቴሌኮም፣ ባንክ እና ሎጅቲክስ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉ በድርጅቱ እንደ ትልቅ ለውጥ የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያን ሕጎች ከድርጅቱ ህጎች ጋር የማጣጣም ስራም ተከናውኗል። ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለው የንግድ ሕግ ማሻሻያ ተደርጎበት ዘመናዊ የንግድ አይነቶች የተካተቱ ሲሆኑ፤ የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መቋቋም የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ላይ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል። ኢትዮጵያ የሸቀጦች ታሪፍ ቅናሽ ሰነዷን አሻሽላ አቅርባለች። ይህም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች የምትጥለው ቀረጥ በምን ያህል መጠንና በስንት ዓመት ውስጥ እንደሚቀንስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የገባችውን ቃል በተግባር ያሳየችበት ነው። በአሁኑ ሰዓት በዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ኢትዮጵያ በተናጠል እንደ ቻይና፣ ሩሲያ፣ አሜሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችና ካናዳ ካሉ ሀገራት እና ከአውሮፓ ህብረት ጋር የገበያ ተደራሽነት ድርድር እያደረገች ነው። በተደረጉት የተናጥል ድርድሮች ላይም ለኢትዮጵያ አባልነት ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። ከአዕምሯዊ ንብረት ጋር በተያያዘ የፈጠራ ውጤቶችን፣ የንግድ ምልክቶችን እና የባህል እሴቶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ ሕግና ተቋም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጓል። የጉምሩክ አሰራር የሸቀጦችን ፍሰት ለማሳለጥ የዲጂታል ጉምሩክ አሰራርን የማስፋፋት ስራ በመንግስት በኩል ተከናውኗል። 14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ስብስባ ከመጋቢት 17 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በካሜሮን ያውንዴ መካሄድ ጀምሯል። በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክም በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ያውንዴ ገብቷል። ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከስብስባው ጎን ለጎን የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን ሚኒስትሩ ከዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ (ዶ/ር) ጋር ያደረጉት ውይይትም በዋናነት የሚጠቀስ ነው። በውይይቱ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለድርጅቱ አባል አገራት ከ1200 በላይ ለሚሆኑ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠቷንና ከ419 በላይ የሕግና የፖሊሲ ይዘቶችን ማሳወቋን ጠቁመዋል። የያውንዴው ስብስባ ለኢትዮጵያ የአባልነት ጉዞ የፖለቲካ ድጋፍን ለማሰባሰብ ያስችላታል። በቅርቡ የድርጅቱ አባል ከሆኑ የአፍሪካ እና ሌሎች ሀገራት ጋር የቴክኒክ እና የተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግም ምቹ አጋጣሚ ይፈጥርላታል። የያውንዴው ውይይት ኢትዮጵያ በቴክኒክ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ ደረጃም ለድርድር ዝግጁ መሆኗን የምታሳይበት ነው። የዓለም የንግድ ድርጅት እ.አ.አ በ1995 የተቋቋመ ሲሆን ዋና መቀመጫው ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ነው።ድርጅቱ 166 አባል ሀገራት አሉት። አባል ሀገራቱ የዓለምን 98 በመቶ የንግድ ልውውጥን እንደሚሸፍኑ መረጃዎች ያመለክታሉ። የዓለም ንግድ ድርጅት በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው አቅምና ተጽዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው። ድርጅቱ ራሱ ገንዘብ የሚያበድር ባንክ ባይሆንም፣ የዓለምን የንግድ “የጨዋታ ሕግ" በመቅረጽ ረገድ ያለው ሚና ትልቅ መሆኑን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል መሆኗ የገበያ እድሏ እንዲሰፋ ያደርጋል። የኢትዮጵያ ምርቶች በ160+ አባል አገራት ገበያ ውስጥ ያለ አድሎና በዝቅተኛ ታሪፍ እንዲገቡ ዕድል ይሰጣል። ይህ በተለይም ለግብርና ውጤቶችና ለጨርቃጨርቅ ምርቶች ትልቅ በር ይከፍታል። የኢትዮጵያ አባል መሆን ሀገሪቷ ዓለም አቀፍ የንግድ ሕጎችን እንደምታከብር ማረጋገጫ ስለሚሆን፤ ትልልቅ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸው እምነት እንዲጨምር ያደርጋል። ኢትዮጵያ አባል መሆኗ ከሌሎች አገራት ጋር የንግድ አለመግባባቶች ቢገጥሟት፣ በድርጅቱ የክርክር መፍቻ መድረክ አማካኝነት መብቷን ማስከበር ትችላለች። ኢትዮጵያ የንግድ አቅሟን ለመገንባት የሚያግዙ ልዩ ልዩ ሥልጠናዎችንና የቴክኒክ ድጋፎችን ከድርጅቱ ማግኘት ትችላለች። ኢትዮጵያ በያዘችው ፍጥነት እና ቁርጠኝነት ከቀጠለች እ.አ.አ 2026 የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድሯን የማጠናቀቅ እድሏ ሰፊ ነው። የድርድሩ መጠናቀቅ ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማጽደቅ እና የአገር ውስጥ ህጎችን ከድርጅቱ ሕግ ጋር የማጣጣም ስራዎችን ጨምሮ በቀጣይ ምዕራፍ ለሚከናወኑ ስራዎች በር ይከፍታል። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን ውጥኗ ከ23 ዓመታት በኋላ እውን ሊሆን የተቃረበ ሲሆን ድርድሩም ወደ መደምደሚያው ምዕራፍ ደርሷል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 904
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል የነዳጅ ብክነትን ለመቀነስ ምን ዓይነት ብልኀት መጠቀም ይመከራል? ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3829
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2598
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8389
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6879
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች
Apr 5, 2026 4407
በዮሐንስ ደርበው ✍️ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ‘በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ’ ከሚለው ብኂል የላቁና ቁጭት የወለዳቸው ኢኒሼቲቮች - የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እንዲሁም የሥራ ዕድልን እያሳደጉ ነው። ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ እንደመሆኗ ብዙ ናት። ይህን ሁሉም ሀገራት ስለማያገኙት ዕድለኛም ናት፤ የእኛም ስለሆነች መታደል ነው። የተለያየ የኑሮ ዘይቤ፣ ባህል እንዲሁም ሁሉንም የዐየር ፀባይ ዐቅፋለች። ደግሞም ልዩ ልዩ የተፈጥሮ አቀማመጥ በልዩነት የተቸራት። አሥረጂ ማቅረብ ቢያሻ በሀገሪቱ ከፍተኛ ከሆነው ስሜን ተራራዎች እስከ ዝቅተኛው ስፍራ ዳሎል ያለውን የተፈጥሮ ፀጋ መጥቀስ ሁነኛ ምሥክር ነው። ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ✍️ የተፈጥሮ ችሮታ ለኢትዮጵያ ከብዙ ሥጦታዎቿ መካከል ብሔራዊ ፓርኮችን ብቻ ብናነሳ… የኢትዮጵያ የዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን በጀት መድቦ በቀጥታ በሥሩ 11 ብሔራዊ ፓርኮችን እና ሁለት የዱር እንስሣት መጠለያዎች ያሥተዳድራል። እነሱም፡- 📌 ስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አብያታ ሻላ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ኦሞ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አልጣሽ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ገራይሌ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ሃላይደጌ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ቃፍታ ሽራሮ ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም 👉 ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ እና 👉 ሲንቂሌ የቆርኬዎች መጠለያዎች ናቸው። ብሔራዊ ፓርኮቹና የዱር እንስሣት መጠለያዎቹ የሀገሬው ሀብት ናቸውና፤ እየተንከባከቡ መጠቀም ይገባል። ✍️ መንግሥት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ከላይ የተገለጹትን ብሔራዊ ፓርኮችና ሌሎችንም፤ ከቤት እንስሣት ንክኪ ነጻ በማድረግ፣ ከልቅ ግጦሽ እንዲሁም ከሕገ-ወጥ ዐደን ለመጠበቅ መንግሥት ብዙ ገንዘብ ያወጣል። የሰው ኃይልና የቁሳቁስ ዐቅርቦትንም ያሟላል። ይህም ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ይመሠክራል። በሌላ በኩል የላሊበላ አብያተክርስቲያናት፣ ሶፍዑመር ዋሻን እና የፋሲል አብያተ መንግሥትን ጨምሮ በየክልሎች የሚገኙ ቅርሶችን በመጠገንም እንዲሁ እየተጋ ነው። ከአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎቹ አንዱ የቱሪዝም ዘርፍ ማድረጉም ትኩረቱን ያሳያል። በዚህ ሂደት በየአካባቢው ፀጋዎችን ዕየለየ በርካታ መዳረሻዎችንና የጎብኝ ማረፊዎችን አልምቷል፤ እያለማም ነው። እነዚህም በኢኮኖሚው ብሎም በሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍ ያለ ሚና እያበረከቱ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት፤ በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ የተሠሩ መዳረሻዎችን ለአብነት ብንጠቅስ፤ ‘በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ’ ከሚለው ብኂል የላቁና ቁጭት የወለዳቸው ኢኒሼቲቮች ናቸው። የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እንዲሁም የሥራ ዕድልን እያሳደጉ ነው። ኢትዮጵያ ዛሬ ነገንም እየሠራች ነውና፤ በቱሪዝሙ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት በተለያየ የኢትዮጵያ ክፍሎች መጭውን ትውልድ ባገናዘበ ሁኔታ እየተሳለጡ ነው። በአፍሪካ መዲና በአንድነት እና የወዳጅነት ፓርኮች ጅማሮውን ያደረገው የዘርፉ ልማት፤ ወደ ወንጪ ኢኮቱሪዝም፣ ጎርጎራ፣ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት፣ የሸበሌ ሪዞርት፣ ሶፍዑመር ዋሻ፣ ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣ የዝሆኖች ዳና ሎጂ፣ የኒዒን ሌ ፓልም ሎጂ ድረስ ወዘተ… ዘልቋል። እንደቀጠለም ነው። እነዚህም ፀጋን ለይቶ ወደ ሃብት በመቀየር ሂደት በመንግሥት ብርታት የለሙ መዳረሻዎች ናቸው። መንግሥት ነባር መዳረሻዎችን በመጠገንና በማደሥ፤ አዳዲስ መዳረሻ በመገንባት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም አልሠሠተም፤ ብዙ እየሠጠ ነው። ✍️ ከቱሪዝም ዘርፍ አንጻር የሕብረተሰቡ ሚና ቱሪዝም በተፈጥሮው ከበርካታ ጉዳዮች ጋር ይተሣሠራል። በእጅጉ ሰላም ይሻል፤ የሰላም ባለቤት ደግሞ ሕዝቡ ነው። ዘርፉ የቅርሶችንና መዳረሻዎችን ልማትና እንክብካቤም ይሻል። ለዘርፉ የሚሰጥ ትኩረት ሀገርንም፤ ሕዝብንም ይጠቅማል፤ ጥቅሙ ከዕለት ጉርስ እስከ ጥሪት ይዘልቃል። በዚህ ሂደት ሕዝቡ በየአካባቢው ያሉ ብሔራዊ ፓርኮችን፣ ቅርሶችን እና የቱሪስት መዳረሻዎችን የኔ ብሎ መጠበቅ ይኖርበታል። ለምሳሌ፡- ብሔራዊ ፓርክ ወይም በመዳረሻ ላይ ጉዳት ቢደርስ በቀጥታ ተጎጂው የአካባቢው ነዋሪ ነው። ምክንያቱም ቱሪስት ካልሄደና ገቢ ካልተገኘ ገቢ ይደርቃልና።
የጀጎል አለም አቀፍ ቅርስን የታደገው ሀገራዊ ለውጥ
Apr 4, 2026 285
የስልጣኔ መነሻ የጥበብ መፍለቂያ የሆነችው የምስራቋ ፈርጥ ሀረር የንግድ፣ የፖለቲካና ማህበራዊ ትስስር ማዕከል ሆና በትውልድ ቅብብሎሽ ከአንድ ሺህ አመታት በላይ የተሻገረች እድሜ ጠገብ ከተማ ነች። በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በምስራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርትና የንግድ ማዕከል የነበረችው ከተማዋ በርካታ ቋሚና ተንቀሳቃሽ እንዲሁም የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቁሳዊና ሀይማኖታዊ ቅርሶችን የያዘች ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ ነች። ከእነዚህ ቅርሶች መካከል ጥንታዊ የስነ-ህንፃ የጥበብ፣ የከተማ ፕላን፣ ባህላዊ የመሬት አጠቃቀም፤ አካባቢያዊ መስተጋብርና የስልጠኔ መገለጫ በሚል እኤአ በ2006 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ዩኔስኮ በአለም አቀፍ ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል ቅርስ ይጠቀሳል፡፡ ቅርሱ ምንም እንኳን በኪነ ህንፃ ጥበብ በላቁ በአርቆ አሳቢ አባቶች እንዳይፈርስና ሚዛኑን ጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ በተመረጠ ድንጋይ እና አፈር በልዩ ጥበብ የተገነባ ቢሆንም በጥበቃና እንክብካቤ ጉድለት ምክንያት ከግማሽ ምዕተ አመታት በላይ እድሜን ባስቆጠረው ቅርስ ላይ አደጋ ተጋርጦበት ቆይቷል። በቅርሱ ውስጣዊ እና ውጫዊ ክፍሎች የህገ-ወጥ ግንባታዎች መበራከትና በሌሎች ምክንያቶች በደረሰበት ጉዳት የጥንት ስልጣኔ ምልክት የሆነው አለም አቀፉ የጀጎል ቅርስ ከዩኔስኮ የአለም ቅርስነት እስከመሰረዝ የደረሰ አደጋ ተደቅኖበት ነበር። ሆኖም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በአዲስ እሳቤ፤ በተደመረ አቅምና በላቀ ቁርጠኝነት፤ ህዝብን በማሳተፍ ከመንግስት ምንም አይነት በጀት ሳይመደብለት ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ማልማት ተቻለ። አሁን ላይ እነኛ በሸራና በጨርቅ በተሰሩ ህገወጥ ግንባታዎች ተወሮ የነበረው 3ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የጀጎል ግንብ ዙሪያ በአበቦችና ቅርሱን በሚያስውቡ ስራዎች ደምቀዋል። በዚህም አባቶች ከዘመኑ ቀድመው ዛሬም ድረስ ግርምትን በሚያጭር ጥበብ አንፀው ያኖሩት ይህንን የሀገር ሀብት በመታደግ ትውልዱን ከታሪክ ተወቃሽነት ወደ ዳግም ታሪክ ሰሪነት እንዲሸጋገር ማድረግ ተችሏል። ስራውም የትላንትን መሰረት ሳያናጋ፤ የቀድሞ አባቶችን ጥበብና ስልጣኔ ሳይጋፋና ሳይዘነጋ ጥንታዊውን ከዘመናዊ ጋር አዋህዶ ቅርስ መገኛ ለሆኑ ሌሎች አካባቢዎችም ተምሳሌት በሚሆን ደረጃ አስደናቂ ስራ ተከናወነ። የአካባቢውን ሀብትና እውቀት በመጠቀም እውን የተደረገው ይህ ስራ በእያንዳንዱ የሀረሪ ጥንታዊ ቤቶች በሚገኙ የታሪክ አሻራዎችና የባህል መገለጫዎች እንዲደምቅም ሆኗል። ይህ ትውልድ ተሻጋሪ ስራ ቅርሱን ከአደጋ ከመታደግ ባለፈ ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከግለሰብ እስከ ማህበራትና የዳያስፖራ አባላት ድረስ ሁሉም በያገባኛል ስሜት አሻራውን ያኖረበት ዘመን ተሻጋሪ ፕሮጀክት ነው። ይህም በቅርሱ ላይ የእኔነት ስሜት እንዲጎለብት በማድረግ የእይታ ለውጥ እንዲመጣ ያስቻለና ቀደም ሲል የነበሩ የግለኝነት አስተሳሰቦችን በመቅረፍ የወል እሳቤ እውን የሆነበት ፕሮጀክት ሆኖ ታይቷል። ዛሬ ላይ እነኛ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ እና በአካባቢው ለማለፍ ከባድ የነበሩ የጀጎል መንገዶች ፀድተው ውብ ሆነዋል። ይዘታቸውን ለቀው የነበሩ ቅርሶችም የአለም ቅርስነት ክብርና መስፈርትን በሚመጥን ደረጃ ታድሰዋል። ዛሬ የጀጎል ነዋሪ እንደቀድሞ አካባቢውን ለቆ ለመሄድ ሳይሆን መኖርን የሚመርጥባት የወጣውም መመለስን የሚመኝባት ምቹ አካባቢ ሆናለች። የመቻል ምልክት የትብብር ውጤትና የአብሮነት ጉልበት በተግባር የታየበት የጁገል መልሶ ልማት ጥንታውን መንደር ለነዋሪዎች ምቹ ለጎብኚዎች ተመራጭ የጉብኝት ስፍራ እንዲሆን ማድረግ ተችሏል። በለውጡ መንግስት በአዲስ መልክና ቀለም የተዋበው ጀጎል የሀረርን ቀደምት ስልጣኔ እየመሰከረ የሀገርንም ገፅታ እየገነባ ይገኛል።