ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎች እየተዘረጉ ነው
Mar 7, 2026 41
አዳማ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በዘላቂነት ለመጠበቅና የዘርፉን አሰራር ለማዘመን የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎችን እየዘረጋ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ገለጸ። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና የኢትዮጵያን የንግድ ምህዳር ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታላቅ ዕድል ነው ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የረቂቅ ደንቡን ይዘት በባለድርሻ አካላት ግብዓት ለማዳበር ያለመ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል። የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በህግ ለመደገፍ አዋጅ ቁጥር 1376/2018 ወጥቶ ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጓል። ይህም የሀገሪቱን የእንስሳትና የእንስሳት ውጤቶች የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳለጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው አሰራር ለመዘርጋት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። አምባሳደር ድሪባ አክለውም፤ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና ምርቱን የሚረከቡ ሀገራት የሚቀበሏቸው የህግ ማዕቀፎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል። አሁን ላይ በእፅዋትና በእንስሳት ዘርፎች አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ስታንዳርዶች ፀድቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የህግ ማዕቀፎቹ የዘርፉ ኢንዱስትሪዎች፣ በተለይም የስጋ አምራቾች ፍላጎትን መሰረት ያደረጉና ከዓለም አቀፍ አሰራር ጋር የተናበቡ እንዲሆኑ ታስቦ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የባለሥልጣኑ የሬጉላቶሪ ዘርፍ ዳይሬክተር ሃሚድ ጀማል (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባለፉት ሰባት ወራት የእንስሳት ምርት ለማምረት ፈቃድ የተሰጣቸውን ተቋማት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የአሰራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውን ገልጸዋል። ምርት ወደ ውጭ ከመላኩ በፊት ከማምረቻው ጀምሮ ጥራትና ደህንነቱ መጠበቅ እንዳለበት ያመለከቱት ዳይሬክተሩ፤ ምርት በቁምም ሆነ ታርዶ ለተጠቃሚው ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ እንዲላክ ተቋሙ ከግብርና ሚኒስቴርና ከባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የባለሥልጣኑ የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አያሌው ሹመት በበኩላቸው፤ የህግ ማዕቀፎቹ የኤክስፖርት ዘርፉን ማነቆዎች የሚቀርፉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ይህም የቁም እንስሳት፣ ስጋ፣ ዶሮ፣ እንቁላል፣ ዓሣ፣ ወተትና የማር ምርቶችን የቁጥጥር አሰራር የሚያዘምን መሆኑን ጠቅሰዋል። በህግ ማዕቀፎቹ ዝግጅት ወቅት የዓለም ንግድ ድርጅትን ጨምሮ የናሚቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ቦትስዋና፣ እንግሊዝና የብራዚል ምርጥ ተሞክሮዎች እንዲካተቱ አድርገናል ሲሉም ገልጸዋል። የህግ ማዕቀፎቹ ተግባራዊ መሆን ለሀገሪቱ የወጭ ንግድ ውጤታማነት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረውም ተመላክቷል።
ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገር ጉዳይ አካታችና አሳታፊ ስርዓት ዘርግቷል
Mar 7, 2026 36
ሀዋሳ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገሩ ጉዳይ አካታችና ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ ስርዓት መዘርጋቱን የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ። ኢትዮጵያን የሚገነባት እና የሚያጸናት የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ ብልፅግና ፓርቲ የማኒፌስቶና የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መድረክ በሀዋሳ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ፤ ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገር ጉዳይ አካታችና ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ ስርዓት መዘርጋቱን አንስተዋል። የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮች ጭምር በሀገር ጉዳይ ላይ ቀጥታ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ስለመሆናቸው ገልጸዋል። ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች እመርታዊ ለውጥና ማንሰራራት የታየባቸው የልማት ስራዎችን ማከናወኑንም ጠቅሰዋል። ፓርቲው ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም መስኮች የህዝብን ተጠቃሚነት እውን ማድረግ የቻሉ የልማት ስኬቶችን ማስመዝገቡንም ተናግረዋል። በስንዴ ልማትና ምርታማነት ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የተቻለበትን እመርታዊ ለውጥና ማንሰራራት በምሳሌነት አንስተው በሌሎች የግብርና ልማት ስራዎችም የላቀ ስኬት ማምጣት ተችሏል ብለዋል። ብልጽግና የዲፕሎማሲ፣ የፖለቲካ፣ ማህበራዊና የምጣኔ ሃብት ስብራቶችን ከመጠገን ባለፈ በኢትዮጵያ ዋልታ ረገጥ እሳቤዎችን በማርገብ ገዥና አሰባሳቢ ትርክት መገንባት ያስቻሉ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል ሲሉ አስረድተዋል። ፓርቲው በቀጣይ ለላቀ ስኬትና የህዝብ ተጠቃሚነት የሚሰራ መሆኑን አቶ ጥራቱ ገልጸዋል። በብልፅግና ፓርቲ የሀዋሳ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ማራዶና ዘለቀ፤ ብልጽግና በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቡ የገባውን ቃል መተግበሩን አስታውሰው በቀጣይም ለላቀ ስኬት መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በለውጡ ዓመታት በተለይም በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ቱሪዝምና ሌሎችም መስኮች የሚያኮሩ ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አንስተው ብልጽግናን መምረጥ የሀገር እድገትንና ስኬትን ማስቀጠል ይሆናል ብለዋል። በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ ማዕከልና የክፍለ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎቸ ተገኝተዋል፡፡
በክልሉ በቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል
Mar 7, 2026 29
ጂንካ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 ዓ/ም ግማሽ ዓመት የስራ አፈፃፀሙን በጂንካ ከተማ እየገመገመ ነው። የቢሮው ኃላፊ ኤካል ነትር በወቅቱ እንደገለፁት፤ ቢሮው በቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት መለወጥ የሚያስችሉ የተቀናጁ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ በተለይም ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ ቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የመስኖ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ የአየር ንብረት ተፅእኖውን በመቋቋም የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ከሚተገበሩ ፕሮጀክቶች መካከል የመስኖ ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም በቆላማ አካባቢዎች ሰፋፊ የመስኖ አውታሮችን በመገንባት አርብቶ አደሩ በግብርና ልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን መደረጉን ገልጸዋል። በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራትም የአንድ ከፍተኛ እና የሁለት መካከለኛ ግድቦች የግንባታ ስራ መጀመሩን ጠቁመው፥ ወደ 8 የሚሆኑ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ደግሞ በተያዘው ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በተያዘው ዓመት ከሚጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መካከል የአርጎባ፣ ብላቴኤታ፣ ማርቃላሾ፣ ሎማቴ እና ሳላ የተሰኙ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ በአካባቢው በመስኖ የማልማት ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ አርብቶ አደሩና ከፊል አርብቶ አደሩን ያማከለ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ማስፋፋት የሚያስችል የጥናትና ዲዛይን ስራ እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል። ከመስኖ ልማት ባሻገር በግጦሽ ሳር ከለላ፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ፣ በንፁህ መጠጥ ውሃና በመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በእንስሳት ግብይት ማዕከላት ግንባታና በሌሎች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ቦሼ ቦምቤ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቢሮው በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ገልፀዋል። አርብቶና ከፊል አርብቶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በዘላቂነት ኑሮውን ለማሻሻል የተጀመረው የመስኖ ልማት እንዲጠናከር የክልሉ መንግስት በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡ በተለይ በግንባታ ላይ ያሉ የመስኖ ፕሮጀክቶች በአጭር ጊዜ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የተቀናጀ ርብርብ እንደሚደረግም ተናግረዋል። የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አብረሃም አታ በበኩላቸው፤ በዞኑ ቆላማ አካባቢዎች የተጀመሩ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች የከፊል አርሶ አደሩን ምርታማነት በማሻሻል በግብርና ልማት ተጠቃሚነቱ እንዲያድግ አድርጓል ብለዋል። የመስኖ ልማት መተግበር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ዓመቱን ሙሉ ለማልማት አቅም በመፈጠሩ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንዳስቻለም ተናግረዋል፡፡
የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከስጋት መታደግ የሚያስችል የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ ይሰራል
Mar 7, 2026 57
አርባ ምንጭ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የስምጥ ሸለቆ ተፋሰስ የሆኑ የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከስጋት ለመታደግ የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ እንደሚሰራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተባባሪነት የአባያና ጫሞ ሀይቆች የሚያስከትሉትን ተጽእኖ መቀነስ የሚያስችል የባለድርሻ አካላት ውይይት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት የአባያና ጫሞ ሀይቆችን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሉ ከፀጋነት ወደ ስጋትነት እየተቀየሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይ በጋሞ፣ በጋርዱላ፣ በኮንሶና በቡርጂ ዞኖች የሚገኙ አርሶ አደሮችን ማሳ እንዲሁም በተለያዩ መሠረተ ልማቶች ላይ አደጋ እያስከተሉ ይገኛሉ ብለዋል። በመሆኑም ሐይቆቹን ከስጋት ለመታደግ የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ እንደሚጠናከር ገልጸዋል፡፡ ተፋሰሶቹ የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር፣ የፍራፍሬ፣ የብዝሃ ህይወት የቱሪዝምና የቀጣናዊ ልማት ማሳለጫዎች መሆናቸውን ጠቅሰው ከስጋት ወደ ሀብት ምንጭነት ለመቀየር የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በውሃው ዘርፍ የረጅም ጊዜ ልምድ ያለው አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉን ችግሮች ለመቅረፍ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው የክልሉ መንግስት የበኩሉን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። የማዕድን ሚኒስትርና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በበኩላቸው የአባያና ጫሞ ሃይቆችን በዘላቂነት መጠቀም ለሃገር ሁለንተናዊ ብልጽግና ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በአርባ ምንጭና አካባቢው መልከ ብዙ ፀጋዎች መኖራቸውን ጠቅሰው የሀይቆቹን ትሩፋት ለማጉላት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በአግባቡ ሊከናወን እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተገኙ ጥናቶች መሠረት የተፋሰሶቹን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ፕሮግራሞች፣ ስትራቴጂዎችና ፕሮጀክቶች ተቀርጸው መተግበር እንዳለባቸውም አመልክተዋል። የአባያና ጫሞ ሀይቆች የውሃ መጠን መጨመር፣ የተፋሰሱ ወንዞች ሙላትና ደለል ከፍተኛ አካባቢያዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎችን እያስከተሉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አብደላ ከማል(ዶ/ር) ናቸው። የአባያና ጫሞ እንዲሁም ሌሎች ተፋሰሶች በተቀናጀ ሁኔታ ካልተመሩ ተጽዕኖው ከሀይቆቹ ዳርቻ አልፎ ሰፊ ቦታዎችን ሊያዳርስ እንደሚችል በጥናት መረጋገጡንም ጠቅሰዋል። ዩኒቨርሲቲው በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች የሚከሰቱ ተግዳሮቶችን በሳይንሳዊ መንገድ ለመከላከል የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የስራ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎችም እየተሳተፉ ነው።
ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ታስተናግዳለች
Mar 7, 2026 37
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ(ASMIS) ልታስተናግድ ነው። ጉባኤውን የሚያዘጋጁት ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ (POA) እና ኤ.ጂ.ኤ ቴክ (AGA-Tech) ኢንተርፕራይዝ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። ጉባኤው እ.አ.አ ግንቦት 7 እና 8 ቀን 2026 በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል። የመጀመሪያ የሆነው ይህ ጉባኤ የአፍሪካ ተፅዕኖ ፈጣሪ ድምፆችን ከመገናኛ ብዙኅን ድርጅቶች፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የግሉ ዘርፍ መሪዎች ጋር የሚያገናኝ ታሪካዊ የጋራ መድረክ መሆኑ ተገልጿል። ''ተፅዕኖ ለተሻለች አፍሪካ'' በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው ጉባኤው የዲጂታል ተሳትፎ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂና ኃላፊነት ላይ ምክክር የሚደረግበት ወሳኝ መድረክ እንደሚሆንም ይጠበቃል። የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ አስተባባሪ በረከት ሲሳይ እንደገለጹት፤ ጉባኤው ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ባለው ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የአፍሪካን የዲጂታል ገጽታና ይዘት ፈጠራ ላይ ትኩረት ያደርጋል ብለዋል። በጉባኤ የቴክኖሎጂ ሥነ-ምኅዳር ፈጠራ፣ የአፍሪካ ታሪክና መፃኢ ተስፋዎች ላይ ጥራት ያላቸው የይዘት ሥራዎችን ለማስተጋባት አቅም የሚፈጠር አህጉራዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሁነቱ በአፍሪካ ሀገራትና በዓለም ዙሪያ የሚሰሩ ከ200 በላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበራዊ ሚዲያ ግለሰቦች ተሰባስበው የሚመክሩበት መሆኑንም ተናግረዋል። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦቹ በዘላቂ ልማት፣ ዲጂታል አስተዳደርና የይዘት ፈጠራ አቅምን የሚያጎለብቱ የምክክርና የትውውቅ መርሃ ግብሮች እንደሚያካሄዱ አብራርተዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት ልምድና ተሞክሮ የሚለዋወጡበት፣ የአፍሪካን ዕድገት በዲጂታል ሥርዓት መግለጥ የሚያስችል እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጠሪዎችን ከትላልቅ የንግድ ድርጅቶች ጋር የሚያገናኝ መድረክ መሆኑንም አንስተዋል። የኤ.ጂ.ኤ ቴክ (AGA-Tech) ኢንተርፕራይዝ አስተባባሪ ባዩሽ ማሞ በበኩላቸው፤ ጉባኤው እያደገ በመጣው የዲጂታል ዓለም የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር ትብብርና ተወዳዳሪነት ለማጎልበት አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሚካሄደው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ይፋዊ ምዝገባ በቅርቡ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። በዚህም የይዘት ፈጣሪዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችና ባለድርሻ አካላት ጉባኤውን የሚመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት በ www.asmis.org ድረ-ገጽን መከታተል እንደሚችሉ ገልጸዋል። የአህጉሪቱን ዲጂታል መጻኢ የፈጠራ አቅምና እጣ ፈንታ በተሻለ ይዘት ለመቅረጽ ጉባአው ወሳኝ መሆኑን ተናግረው ታላላቅ የንግድ ተቋማትና ድርጅቶችም ለጉባኤው ስኬታማነት በአጋርነት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ፖለቲካ
ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገር ጉዳይ አካታችና አሳታፊ ስርዓት ዘርግቷል
Mar 7, 2026 36
ሀዋሳ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገሩ ጉዳይ አካታችና ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ ስርዓት መዘርጋቱን የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ። ኢትዮጵያን የሚገነባት እና የሚያጸናት የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ ብልፅግና ፓርቲ የማኒፌስቶና የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መድረክ በሀዋሳ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ፤ ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገር ጉዳይ አካታችና ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ ስርዓት መዘርጋቱን አንስተዋል። የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮች ጭምር በሀገር ጉዳይ ላይ ቀጥታ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ስለመሆናቸው ገልጸዋል። ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች እመርታዊ ለውጥና ማንሰራራት የታየባቸው የልማት ስራዎችን ማከናወኑንም ጠቅሰዋል። ፓርቲው ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም መስኮች የህዝብን ተጠቃሚነት እውን ማድረግ የቻሉ የልማት ስኬቶችን ማስመዝገቡንም ተናግረዋል። በስንዴ ልማትና ምርታማነት ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የተቻለበትን እመርታዊ ለውጥና ማንሰራራት በምሳሌነት አንስተው በሌሎች የግብርና ልማት ስራዎችም የላቀ ስኬት ማምጣት ተችሏል ብለዋል። ብልጽግና የዲፕሎማሲ፣ የፖለቲካ፣ ማህበራዊና የምጣኔ ሃብት ስብራቶችን ከመጠገን ባለፈ በኢትዮጵያ ዋልታ ረገጥ እሳቤዎችን በማርገብ ገዥና አሰባሳቢ ትርክት መገንባት ያስቻሉ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል ሲሉ አስረድተዋል። ፓርቲው በቀጣይ ለላቀ ስኬትና የህዝብ ተጠቃሚነት የሚሰራ መሆኑን አቶ ጥራቱ ገልጸዋል። በብልፅግና ፓርቲ የሀዋሳ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ማራዶና ዘለቀ፤ ብልጽግና በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቡ የገባውን ቃል መተግበሩን አስታውሰው በቀጣይም ለላቀ ስኬት መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በለውጡ ዓመታት በተለይም በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ቱሪዝምና ሌሎችም መስኮች የሚያኮሩ ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አንስተው ብልጽግናን መምረጥ የሀገር እድገትንና ስኬትን ማስቀጠል ይሆናል ብለዋል። በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ ማዕከልና የክፍለ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎቸ ተገኝተዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መራጮች የምርጫ ካርድ መውሰድ ጀምረዋል
Mar 7, 2026 103
ጭሮ፣ ነጌሌ ቦረና፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መራጮች በየምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ካርድ መውሰድ ጀምረዋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ዛሬ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሯል። በጊዜ ሰሌዳው መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከተጀመረባቸው የኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መካከል ምዕራብ ሀረርጌ ዞን ጭሮ፣ ምስራቅ ቦረና ነጌሌ፣ ምስራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተሞች ይጠቀሳሉ። ኢዜአ በጭሮ ከተማ የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኛቸው ነዋሪዎች በምርጫው በንቃት ለመሳተፍ ቀድመው የምርጫ ካርድ በመውስድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በከተማው የቡርቃ ጭሮ ቀበሌ ነዋሪ ከድር ሰይድ እንዳሉት፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱ የተያያዘችውን እድገትና ብልፅግና ከዳር ለሚያደርስ ተወዳዳሪ ድምፃቸውን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። የዴሞክራሲ ስርዓት መሰረት የሚይዘው እና የሀገር ዕድገት የሚረጋገጠው በምርጫ በመሆኑ በንቃት እንደሚሳተፉ ተናግረዋል። ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ይወክለኛል የሚሉትን ተወዳዳሪ ለመምረጥ መመዝገባቸውን የተናገሩት ደግሞ በከተማው ጨፌ አራራ ቀበሌ ነዋሪ መሐመድ ሐሰን ናቸው። ''ባለፉት አራት ተከታታይ ምርጫዎች ተሳትፌያለሁ'' የሚሉት አስተያየት ሰጪው የዘንድሮው ምርጫ የሀገሪቱን የዕድገት ጉዞ ለማፋጠን ወሳኝ በመሆኑ በትኩረትና በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ መብቱን ተጠቅሞ ቀድሞ በመመዝገብ ለሚፈልገው አካል ድምፁን ሊሰጥ እንደሚገባም አመልክተዋል። በምስራቅ ቦረና ዞን የነገሌ ቦረና ከተማ ነዋሪ ወይዘሪት ገሊላ ፍቃዱ፤ በነገሌ ምርጫ ክልል ከሀሎ ጋፍትሮ ምርጫ ጣቢያ የመራጭነት ካርድ ወስደዋል፡፡ ካርድ የወሰዱት በመጪው ግንቦት ወር በሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ለአብሮነት፣ ለሰላም፣ ለልማትና ለሀገራዊ እድገት ይሰራል ለምትለው ፓርቲና እጩ ተወዳዳሪ ድምጽ ለመስጠት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሁሉም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በሀገራዊ ምርጫው በመሳተፍ ለሚፈልገው ፓርቲ ድምጹን እንዲሰጥም መክረዋል፡፡ በምስራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ ቡርቃ ጃቶ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ፈይሳ ጭምዴሳ፣ በጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። ሌሎችም ሀገርንና ህዝብን የበለጠ ተጠቃሚ የሚያደርግ የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ እንዲችሉ በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ካርድ እንዲወስዱም አመልክተዋል።
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የድርሻችንን እንወጣለን- የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች
Mar 7, 2026 55
ቦንጋ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና አንድነትን የሚያመጣ በመሆኑ ለስኬታማነቱ የድርሻቸውን እንደሚወጡ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠርና የአገረ መንግሥት ግንባታን ለማጽናት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል በሀገሪቱ ስር የሰደዱ አለመግባባቶችና ልዩነቶች አካታችና አሳታፊ በሆነ መንገድ ለመፍታት፣ ዘላቂ ስላምንና አንድነትን ለማምጣት እንዲቻል የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ እየተሰራ ነው። ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት የአጀንዳ ልየታ ስራውን በማጠናቀቅ ወደ ዋናው ምክክር የሚያስገቡ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የቦንጋ ከተማ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች፤ ምክክሩ በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባትና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ፋይዳው የላቀ በመሆኑ ለስኬታማነቱ እንሰራለን ብለዋል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሃይማኖት አባት የሆኑት መጋቤ ሀይማኖት እሸቱ በላይ ፤ በመመካከርና ተቀራርቦ በመነጋገር የማይፈታ ችግር፣ የማንሻገረው ፈተና ባለመኖሩ የሰላምን መንገድ መከተል ይገባል ብለዋል። የምክክር ኮሚሽኑ መቋቋም በተለያዩ ጊዜያት የተፈጠሩና ስር የሰደዱ ቅራኔዎችና አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ኢትዮጵያን በልማት ቀዳሚ ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን ገልፀዋል። ለዚህም የኮሚሽኑን ስራ መደገፍና የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ከሁሉም ዜጋ የሚጠበቅ በመሆኑ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አመልክተዋል። የካፋ ዞን የወንጌል አማኞች ካውንስል ዋና ፀሐፊ ፓስተር መለሰ እንዳለ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ በኢትዮጵያ ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮች ተፈተው ዜጎች የተረጋጋና ምቹ ሕይወት እንዲመሩ ሰፊ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል። በምክክሩ ያሉብንን ልዩነቶች ተቀራርበን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት ሰላሟ የተረጋገጠና የበለፀገች ሀገርን ለትውልድ ማስተላለፍ ይጠበቅብናል ነው ያሉት። ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን ተመካክሮ በመፍታት መተማመን መፍጠር ይቻላል ያሉት ደግሞ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ ኡስታዝ ሸረፈዲን ኑሩ ናቸው። ኮሚሽኑ የሚያከናውናቸውን ተግባራት መደገፍም ሰላምና አንድነትን የሚያመጣ በመሆኑ የሐይማኖት ተቋማት ዋነኛ ተግባራችን አድርገን የምንሔድበት ተልዕኮ ነው ብለዋል። በሀገሪቱ አሳታፊና አካታች ምክክር የማድረግ ልምድ ባለመኖሩ መሰረታዊ በሚባሉ ጉዳዮች ላይ ሲፈጠሩ የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት አዳጋች እንደነበር ያስታውሱት ደግሞ የሀገር ሽማግሌ አቶ ወርቁ ወልደማርያም ናቸው። በአሁኑ ወቅትም ማሕበረሰቡ የምክክር ኮሚሽኑ በሚያከናውናቸው ተግባራት ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ለማድረግ የሚጠበቅብኝን ሚና ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብለዋል። የሀገር ሽማግሌና የካፋ ባህል ምክር ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ በየነ በቀለ በበኩላቸው፤ ምክክሩ ለዘመናት ሀገራችንን ወደ ኋላ ሲጎትቱ የቆዩ ችግሮችን በጋራ ተነጋግሮ በመፍታት ወደ ፊት ለመራመድ የሚያስችለንን እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ በሁሉም አካባቢዎች ያለምንም ልዩነት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ባሳተፈና ባካተተ መልኩ ውይይቶችን ሲያካሄድ መቆየቱ የራሳችንን ችግር በራሳችን ለመፍታት እንደምንችል ያሳየና አዲስ ልምምድን ያመጣ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር በሃሳብ ልዩነታችን ውስጥ የማንደራደርበት ቀይ መስመራችን ነው - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Mar 7, 2026 118
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር በሀገራዊ የፖለቲካ የሃሳብ ልዩነታቸው ውስጥ ለድርድር የማይቀርብ ቀይ መስመር መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ብሔራዊ ጥቅም የሀገርን ሉዓላዊ የግዛት አንድነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የማኅበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚተለም የጋራ መሰረተ-ሕግና ታላቅ ሀገራዊ ግብ ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ፅንሰ ሀሳቦች ላይ ማተኮር ይጠበቅባቸዋል - ምሁራን ለዚህም የአንድ ሀገር ዜጎች፣ መንግስትና የፖለቲካ አደረጃጀቶች በሃሳብ ልዩነት ውስጥ በዋና ዋና መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅ የሚያችል የጋራ አቋም ሊይዙ ግድ ይላል። ኢትዮጵያና ዜጎቿም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና የቴክኖሎጂ መስኮች ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎቶችን የሚያስጠበቁ ሁለንተናዊ አቅም እየገነቡ ይገኛል። በአሁኑ ወቅትም በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስቀጠል የባሕር በር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የዲፕሎማሲ ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ስኬታማነትም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር ጠንካራ ሀገረ መንግስት የሚያንጹ የጋራ አጀንዳዎችና መሰረቶች ናቸው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደገለጹት፤ የሀገር ብሔራዊ ጥቅሞች በፖለቲካ እሳቤና የሃሳብ ልዩነቶች የማይገደቡ የሁሉም ዜጎች የማይታለፉ የጋራ አጀንዳዎች ናቸው ብለዋል። የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች ማስከበር በፖለቲካ የሃሳብ ልዩነት ውስጥ ለድርድር የማይቀርቡ ቀይ መስመሮች መሆናቸውን ገልጸዋል። ከኢትዮጵያ ውጭ ሌላ ሀገር የለንም ያሉት ኃላፊዋ፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይም ልዩነት ሊኖረን አይገባም ብለዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ማንኛውም የፖለቲካ አደረጃጀትና ዜጋ በአንድነት ሊቆሙለት የሚገባ የጋራ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮምኑኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ ጣዕመ አርዓዶም በበኩላቸው፤ ብሔራዊ ጥቅም ከማንኛውም የሃሳብ ልዩነቶች በላይ የጋራ አጀንዳ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር ብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ መሳሪያ መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞች በማንኛውም አይነት የፖለቲካና የሃሳብ ልዩነቶች ውስጥ ለድርድር ሊቀርቡ እንደማይገባ ተናግረዋል። በዚህም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ፓርቲያቸው የበኩሉን ገንቢ ሚና ለመወጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ሰለሞን ታፈሰም እንዲሁ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞች በምንም አይነት መንገድ ለድርድር የማይቀርቡ የጋራ ጉዳዮቻችን ናቸው ብለዋል። ለአብነትም የባሕር በር ባለቤትነት ማስከበርና ሀገራዊ ምክክር፣ ዘላቂ ልማትና ሰላም ግንባታ የኢትዮጵያ ለድርድር የማይቀርቡ የጋራ ብሔራዊ ጥቅሞች መሆናቸውን በመግለጽ። በዚህም የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነትና ሀገራዊ ምክክር በስኬት በመቋጨት አስተማማኝ ዕድገትን የሚያስቀጥል ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
ለመራጭነት የሚያበቃንን ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል -የጂንካ ከተማ ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 101
ጂንካ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን የጂንካ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ፅንሰ ሀሳቦች ላይ ማተኮር ይጠበቅባቸዋል - ምሁራን አስተያየታቸውን የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች፤ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ቦጋለ ታደሰ ቀድመው የምርጫ ካርድ በመውስድ በምርጫው ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በምርጫ ሂደት የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ሰው በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበትም መልዕክት አስተላልፈዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሰመረ በላይ በበኩላቸው፤ ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በምርጫው ''ይበጀኛል፣ ይወክለኛል፣ ይመራኛል'' የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ሴቶች በምርጫው ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በማበረታታት ላይ እንደሚገኙ የተናገሩት ደግሞ ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ፤ ሴቶች በምርጫው እንዲሳተፉ ግንዛቤ የማስጨበጥና የማስተባበር ሥራ እየሠሩ መሆኑን ገልጸዋል። እሳቸውም ድምፅ ለመስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ወጣት ጌታያውቃል ያለው በበኩሉ ወጣቶች በሀገራቸው ጉዳይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸው ጠቅሶ እሱም የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሚናውን ከመወጣት ባለፈ የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀቱን አስረድቷል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ፅንሰ ሀሳቦች ላይ ማተኮር ይጠበቅባቸዋል - ምሁራን
Mar 7, 2026 111
ሆሳዕና ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ፅንሰ ሀሳቦች ላይ ማተኮር እንደሚጠበቅባቸው የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ገለፁ፡፡ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ቅስቀሳ ጨምሮ የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ነው፡፡ ኢዜአ በፖለቲካ ፓርቲዎች ቅስቀሳ አካሄድ ዙሪያ ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር ቆይታ አድርጓል። ምሁራኑ በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሃገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ጽንሰ ሃሳቦች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ አበራ ሄቢሶ እንዳሉት፤ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሀሳብን ይዘው በመቅረብ ሀገርን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ጉዳዮችን ሊያነሱ ይገባል፡፡ የሀገረ መንግሥት ግንባታው የሚጠናከረው በሁሉም ኢትዮጵያውያን ይሁንታና ቅቡልነት በመሆኑ ገዥ ትርክትን በማስረጽ በጋራ ለመበልጸግ የሚደረገውን ጥረት ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከወገንተኝነት አስተሳሰብና ከፋፋይ ትርክት በመውጣት የህዝብ ፍላጎትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚረዱ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች ላይ በማተኮር በህዝቡ ቅቡልነት ለማግኘት መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተፈጠረውን ምቹ ስነ-ምህዳር በመጠቀም ሃገራዊ ጥቅምን ያስቀደሙ ጽንሰ ሃሳቦች ላይ ማተኮር አለባቸው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሳምሶን ወልዴ ናቸው።፡ ለሀገርና ለህዝብ ጠቃሚ የሆኑ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን ለህዝቡ በማቅረብ በውድድሩ ተቀባይነትን ለማግኘትና ለጋራ ተጠቃሚነት መረጋገጥ መስራት ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ ይጠበቃል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ነው።
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል
Mar 6, 2026 134
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዝግጅት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ገለጹ። 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ በተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የመራጮች ምዝገባ ከነገ ጀምሮ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመራጮች ምዝገባ ለአንድ ወር እንደሚካሄድ ገልጸው፤ ምዝገባው በዲጂታል እና በማንዋል መልኩ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል። ከፕሌይ ስቶርና አፕ ስቶር "ምርጫዬ" የተሰኘውን መተግበሪያ አውርደው በስልካቸው መመዝገብ የሚችሉ ዜጎች በራሳቸው መመዝገብ እንደሚችሉም ጠቁመዋል። በአካል ምርጫ ጣቢያዎች የሚመዘገቡ መራጮችን ለማስተናገድም ቦርዱ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ታብሌቶችን ማሰራጨቱን አብራርተዋል። ከ3 ጂ በላይ ኢንተርኔት ተደራሽነት ባለባቸው አካበቢዎች የመራጮች ምዝገባው በዲጂታል እንደሚደረግ ጠቁመው፤ ለዚህም ቦርዱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን ማስመዝገባቸውን አክለዋል። ከዚህ ውስጥ 2ሺህ 198 ዕጩዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመዘገቡ ሲሆን 8 ሺህ 736 ለክልል ምክር ቤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ እንዳሉት 73 በግል በዕጩነት የቀረቡ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 69ኙ ወንድ 4ቱ ደግሞ ሴት ዕጩዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቦርዱ ፓርቲዎች የሚወዳደሩበትን ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብንም ፓርቲዎች እንዲፈርሙ መደረጉን ከቅድመ ዝግጅት ስራዎች መካከል መሆኑን አብራርተዋል።
ለመራጭነት የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህርዳርና የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ
Mar 6, 2026 84
ባህር ዳር/ጀረር፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህር ዳር ከተማ እና በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሔደው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ ተአማኒና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። መራጮች መዝገባም ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀመር ቦርዱ ያሳወቀ ሲሆን ኢዜአም በባህርዳር ከተማና እና በሶማሌ ክልል ጀረር ዞን ከተሞች ነዋሪዎች መምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ ያላቸውን ዝግጁነት በማስመልከት አነጋግሯል። በባህር ዳር ከተማ ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎቹ መካከል አቶ ሰይፈአርዕድ ሙሏለም እንደገለጹት ዘንድሮ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይመራኛል፤ ያስተዳድረኛል ብለው ያመኑበትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ እየተዘጋጁ ነው። እንደሀገር ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች በንቃት በመሳተፍ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መብታቸውን ማረጋገጣቸውን አስታውሰዋል። ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝግባም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በምርጫው እለት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ፣ ሀገረ መንግስቱን ለማጽናትና ልማትን ለማፋጠን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊና ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ነዋሪዋ፣ ህብረተሰቡ በምርጫው ለመሳተፍ በወቅቱ በመመዝገብ የመራጭነት ካርድ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ማረጋገጥና የፈለግነውን ፓርቲ መምረጥ የምንችለው የምርጫ ካርድ በወቅቱ ስንይዝ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ አማረ ጌጡ ናቸው። በተመሳሳይ በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎችም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የዞኑ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ሃይብ ሳላህ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ቀኑን እየተጠባበቁ ናቸው። በተለይ የሴቶችን እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። "በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይሆነኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቺያለሁ" ያሉት ደግሞ አቶ አብዱላሂ ዊል መሀሙድ ናቸው። በተለይ ለአገር አድገት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥና ተግቶ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ምርጫቸው መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም በነገው እለት የመራጮች ምዝገባ ካርድ ለመውስድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ከአጠቃላይ የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17 ሺህ ያህሉ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
ፖለቲካ
ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገር ጉዳይ አካታችና አሳታፊ ስርዓት ዘርግቷል
Mar 7, 2026 36
ሀዋሳ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገሩ ጉዳይ አካታችና ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ ስርዓት መዘርጋቱን የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ። ኢትዮጵያን የሚገነባት እና የሚያጸናት የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ ብልፅግና ፓርቲ የማኒፌስቶና የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መድረክ በሀዋሳ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ፤ ብልጽግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ በሀገር ጉዳይ አካታችና ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ ስርዓት መዘርጋቱን አንስተዋል። የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮች ጭምር በሀገር ጉዳይ ላይ ቀጥታ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ስለመሆናቸው ገልጸዋል። ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች እመርታዊ ለውጥና ማንሰራራት የታየባቸው የልማት ስራዎችን ማከናወኑንም ጠቅሰዋል። ፓርቲው ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም መስኮች የህዝብን ተጠቃሚነት እውን ማድረግ የቻሉ የልማት ስኬቶችን ማስመዝገቡንም ተናግረዋል። በስንዴ ልማትና ምርታማነት ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የተቻለበትን እመርታዊ ለውጥና ማንሰራራት በምሳሌነት አንስተው በሌሎች የግብርና ልማት ስራዎችም የላቀ ስኬት ማምጣት ተችሏል ብለዋል። ብልጽግና የዲፕሎማሲ፣ የፖለቲካ፣ ማህበራዊና የምጣኔ ሃብት ስብራቶችን ከመጠገን ባለፈ በኢትዮጵያ ዋልታ ረገጥ እሳቤዎችን በማርገብ ገዥና አሰባሳቢ ትርክት መገንባት ያስቻሉ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል ሲሉ አስረድተዋል። ፓርቲው በቀጣይ ለላቀ ስኬትና የህዝብ ተጠቃሚነት የሚሰራ መሆኑን አቶ ጥራቱ ገልጸዋል። በብልፅግና ፓርቲ የሀዋሳ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ማራዶና ዘለቀ፤ ብልጽግና በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቡ የገባውን ቃል መተግበሩን አስታውሰው በቀጣይም ለላቀ ስኬት መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በለውጡ ዓመታት በተለይም በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ቱሪዝምና ሌሎችም መስኮች የሚያኮሩ ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አንስተው ብልጽግናን መምረጥ የሀገር እድገትንና ስኬትን ማስቀጠል ይሆናል ብለዋል። በመድረኩ የሀዋሳ ከተማ ማዕከልና የክፍለ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎቸ ተገኝተዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መራጮች የምርጫ ካርድ መውሰድ ጀምረዋል
Mar 7, 2026 103
ጭሮ፣ ነጌሌ ቦረና፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መራጮች በየምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ካርድ መውሰድ ጀምረዋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ዛሬ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሯል። በጊዜ ሰሌዳው መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከተጀመረባቸው የኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መካከል ምዕራብ ሀረርጌ ዞን ጭሮ፣ ምስራቅ ቦረና ነጌሌ፣ ምስራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተሞች ይጠቀሳሉ። ኢዜአ በጭሮ ከተማ የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኛቸው ነዋሪዎች በምርጫው በንቃት ለመሳተፍ ቀድመው የምርጫ ካርድ በመውስድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በከተማው የቡርቃ ጭሮ ቀበሌ ነዋሪ ከድር ሰይድ እንዳሉት፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱ የተያያዘችውን እድገትና ብልፅግና ከዳር ለሚያደርስ ተወዳዳሪ ድምፃቸውን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። የዴሞክራሲ ስርዓት መሰረት የሚይዘው እና የሀገር ዕድገት የሚረጋገጠው በምርጫ በመሆኑ በንቃት እንደሚሳተፉ ተናግረዋል። ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ይወክለኛል የሚሉትን ተወዳዳሪ ለመምረጥ መመዝገባቸውን የተናገሩት ደግሞ በከተማው ጨፌ አራራ ቀበሌ ነዋሪ መሐመድ ሐሰን ናቸው። ''ባለፉት አራት ተከታታይ ምርጫዎች ተሳትፌያለሁ'' የሚሉት አስተያየት ሰጪው የዘንድሮው ምርጫ የሀገሪቱን የዕድገት ጉዞ ለማፋጠን ወሳኝ በመሆኑ በትኩረትና በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ መብቱን ተጠቅሞ ቀድሞ በመመዝገብ ለሚፈልገው አካል ድምፁን ሊሰጥ እንደሚገባም አመልክተዋል። በምስራቅ ቦረና ዞን የነገሌ ቦረና ከተማ ነዋሪ ወይዘሪት ገሊላ ፍቃዱ፤ በነገሌ ምርጫ ክልል ከሀሎ ጋፍትሮ ምርጫ ጣቢያ የመራጭነት ካርድ ወስደዋል፡፡ ካርድ የወሰዱት በመጪው ግንቦት ወር በሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ለአብሮነት፣ ለሰላም፣ ለልማትና ለሀገራዊ እድገት ይሰራል ለምትለው ፓርቲና እጩ ተወዳዳሪ ድምጽ ለመስጠት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሁሉም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በሀገራዊ ምርጫው በመሳተፍ ለሚፈልገው ፓርቲ ድምጹን እንዲሰጥም መክረዋል፡፡ በምስራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ ቡርቃ ጃቶ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ፈይሳ ጭምዴሳ፣ በጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። ሌሎችም ሀገርንና ህዝብን የበለጠ ተጠቃሚ የሚያደርግ የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ እንዲችሉ በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ካርድ እንዲወስዱም አመልክተዋል።
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የድርሻችንን እንወጣለን- የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች
Mar 7, 2026 55
ቦንጋ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና አንድነትን የሚያመጣ በመሆኑ ለስኬታማነቱ የድርሻቸውን እንደሚወጡ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠርና የአገረ መንግሥት ግንባታን ለማጽናት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል በሀገሪቱ ስር የሰደዱ አለመግባባቶችና ልዩነቶች አካታችና አሳታፊ በሆነ መንገድ ለመፍታት፣ ዘላቂ ስላምንና አንድነትን ለማምጣት እንዲቻል የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ እየተሰራ ነው። ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት የአጀንዳ ልየታ ስራውን በማጠናቀቅ ወደ ዋናው ምክክር የሚያስገቡ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የቦንጋ ከተማ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች፤ ምክክሩ በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባትና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ፋይዳው የላቀ በመሆኑ ለስኬታማነቱ እንሰራለን ብለዋል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሃይማኖት አባት የሆኑት መጋቤ ሀይማኖት እሸቱ በላይ ፤ በመመካከርና ተቀራርቦ በመነጋገር የማይፈታ ችግር፣ የማንሻገረው ፈተና ባለመኖሩ የሰላምን መንገድ መከተል ይገባል ብለዋል። የምክክር ኮሚሽኑ መቋቋም በተለያዩ ጊዜያት የተፈጠሩና ስር የሰደዱ ቅራኔዎችና አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ኢትዮጵያን በልማት ቀዳሚ ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን ገልፀዋል። ለዚህም የኮሚሽኑን ስራ መደገፍና የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ከሁሉም ዜጋ የሚጠበቅ በመሆኑ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አመልክተዋል። የካፋ ዞን የወንጌል አማኞች ካውንስል ዋና ፀሐፊ ፓስተር መለሰ እንዳለ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ በኢትዮጵያ ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮች ተፈተው ዜጎች የተረጋጋና ምቹ ሕይወት እንዲመሩ ሰፊ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል። በምክክሩ ያሉብንን ልዩነቶች ተቀራርበን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት ሰላሟ የተረጋገጠና የበለፀገች ሀገርን ለትውልድ ማስተላለፍ ይጠበቅብናል ነው ያሉት። ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን ተመካክሮ በመፍታት መተማመን መፍጠር ይቻላል ያሉት ደግሞ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ ኡስታዝ ሸረፈዲን ኑሩ ናቸው። ኮሚሽኑ የሚያከናውናቸውን ተግባራት መደገፍም ሰላምና አንድነትን የሚያመጣ በመሆኑ የሐይማኖት ተቋማት ዋነኛ ተግባራችን አድርገን የምንሔድበት ተልዕኮ ነው ብለዋል። በሀገሪቱ አሳታፊና አካታች ምክክር የማድረግ ልምድ ባለመኖሩ መሰረታዊ በሚባሉ ጉዳዮች ላይ ሲፈጠሩ የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት አዳጋች እንደነበር ያስታውሱት ደግሞ የሀገር ሽማግሌ አቶ ወርቁ ወልደማርያም ናቸው። በአሁኑ ወቅትም ማሕበረሰቡ የምክክር ኮሚሽኑ በሚያከናውናቸው ተግባራት ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ለማድረግ የሚጠበቅብኝን ሚና ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብለዋል። የሀገር ሽማግሌና የካፋ ባህል ምክር ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ በየነ በቀለ በበኩላቸው፤ ምክክሩ ለዘመናት ሀገራችንን ወደ ኋላ ሲጎትቱ የቆዩ ችግሮችን በጋራ ተነጋግሮ በመፍታት ወደ ፊት ለመራመድ የሚያስችለንን እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ በሁሉም አካባቢዎች ያለምንም ልዩነት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ባሳተፈና ባካተተ መልኩ ውይይቶችን ሲያካሄድ መቆየቱ የራሳችንን ችግር በራሳችን ለመፍታት እንደምንችል ያሳየና አዲስ ልምምድን ያመጣ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር በሃሳብ ልዩነታችን ውስጥ የማንደራደርበት ቀይ መስመራችን ነው - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Mar 7, 2026 118
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር በሀገራዊ የፖለቲካ የሃሳብ ልዩነታቸው ውስጥ ለድርድር የማይቀርብ ቀይ መስመር መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ብሔራዊ ጥቅም የሀገርን ሉዓላዊ የግዛት አንድነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የማኅበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚተለም የጋራ መሰረተ-ሕግና ታላቅ ሀገራዊ ግብ ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ፅንሰ ሀሳቦች ላይ ማተኮር ይጠበቅባቸዋል - ምሁራን ለዚህም የአንድ ሀገር ዜጎች፣ መንግስትና የፖለቲካ አደረጃጀቶች በሃሳብ ልዩነት ውስጥ በዋና ዋና መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅ የሚያችል የጋራ አቋም ሊይዙ ግድ ይላል። ኢትዮጵያና ዜጎቿም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና የቴክኖሎጂ መስኮች ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎቶችን የሚያስጠበቁ ሁለንተናዊ አቅም እየገነቡ ይገኛል። በአሁኑ ወቅትም በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስቀጠል የባሕር በር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የዲፕሎማሲ ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ስኬታማነትም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር ጠንካራ ሀገረ መንግስት የሚያንጹ የጋራ አጀንዳዎችና መሰረቶች ናቸው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደገለጹት፤ የሀገር ብሔራዊ ጥቅሞች በፖለቲካ እሳቤና የሃሳብ ልዩነቶች የማይገደቡ የሁሉም ዜጎች የማይታለፉ የጋራ አጀንዳዎች ናቸው ብለዋል። የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች ማስከበር በፖለቲካ የሃሳብ ልዩነት ውስጥ ለድርድር የማይቀርቡ ቀይ መስመሮች መሆናቸውን ገልጸዋል። ከኢትዮጵያ ውጭ ሌላ ሀገር የለንም ያሉት ኃላፊዋ፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይም ልዩነት ሊኖረን አይገባም ብለዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ማንኛውም የፖለቲካ አደረጃጀትና ዜጋ በአንድነት ሊቆሙለት የሚገባ የጋራ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮምኑኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ ጣዕመ አርዓዶም በበኩላቸው፤ ብሔራዊ ጥቅም ከማንኛውም የሃሳብ ልዩነቶች በላይ የጋራ አጀንዳ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር ብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ መሳሪያ መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞች በማንኛውም አይነት የፖለቲካና የሃሳብ ልዩነቶች ውስጥ ለድርድር ሊቀርቡ እንደማይገባ ተናግረዋል። በዚህም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ፓርቲያቸው የበኩሉን ገንቢ ሚና ለመወጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ሰለሞን ታፈሰም እንዲሁ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞች በምንም አይነት መንገድ ለድርድር የማይቀርቡ የጋራ ጉዳዮቻችን ናቸው ብለዋል። ለአብነትም የባሕር በር ባለቤትነት ማስከበርና ሀገራዊ ምክክር፣ ዘላቂ ልማትና ሰላም ግንባታ የኢትዮጵያ ለድርድር የማይቀርቡ የጋራ ብሔራዊ ጥቅሞች መሆናቸውን በመግለጽ። በዚህም የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነትና ሀገራዊ ምክክር በስኬት በመቋጨት አስተማማኝ ዕድገትን የሚያስቀጥል ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
ለመራጭነት የሚያበቃንን ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል -የጂንካ ከተማ ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 101
ጂንካ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን የጂንካ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ፅንሰ ሀሳቦች ላይ ማተኮር ይጠበቅባቸዋል - ምሁራን አስተያየታቸውን የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች፤ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ቦጋለ ታደሰ ቀድመው የምርጫ ካርድ በመውስድ በምርጫው ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በምርጫ ሂደት የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ሰው በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበትም መልዕክት አስተላልፈዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሰመረ በላይ በበኩላቸው፤ ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በምርጫው ''ይበጀኛል፣ ይወክለኛል፣ ይመራኛል'' የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ሴቶች በምርጫው ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በማበረታታት ላይ እንደሚገኙ የተናገሩት ደግሞ ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ፤ ሴቶች በምርጫው እንዲሳተፉ ግንዛቤ የማስጨበጥና የማስተባበር ሥራ እየሠሩ መሆኑን ገልጸዋል። እሳቸውም ድምፅ ለመስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ወጣት ጌታያውቃል ያለው በበኩሉ ወጣቶች በሀገራቸው ጉዳይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸው ጠቅሶ እሱም የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሚናውን ከመወጣት ባለፈ የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀቱን አስረድቷል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ፅንሰ ሀሳቦች ላይ ማተኮር ይጠበቅባቸዋል - ምሁራን
Mar 7, 2026 111
ሆሳዕና ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ፅንሰ ሀሳቦች ላይ ማተኮር እንደሚጠበቅባቸው የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ገለፁ፡፡ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ቅስቀሳ ጨምሮ የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ነው፡፡ ኢዜአ በፖለቲካ ፓርቲዎች ቅስቀሳ አካሄድ ዙሪያ ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር ቆይታ አድርጓል። ምሁራኑ በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሃገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚረዱ ጽንሰ ሃሳቦች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ አበራ ሄቢሶ እንዳሉት፤ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሀሳብን ይዘው በመቅረብ ሀገርን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ጉዳዮችን ሊያነሱ ይገባል፡፡ የሀገረ መንግሥት ግንባታው የሚጠናከረው በሁሉም ኢትዮጵያውያን ይሁንታና ቅቡልነት በመሆኑ ገዥ ትርክትን በማስረጽ በጋራ ለመበልጸግ የሚደረገውን ጥረት ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከወገንተኝነት አስተሳሰብና ከፋፋይ ትርክት በመውጣት የህዝብ ፍላጎትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚረዱ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች ላይ በማተኮር በህዝቡ ቅቡልነት ለማግኘት መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተፈጠረውን ምቹ ስነ-ምህዳር በመጠቀም ሃገራዊ ጥቅምን ያስቀደሙ ጽንሰ ሃሳቦች ላይ ማተኮር አለባቸው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሳምሶን ወልዴ ናቸው።፡ ለሀገርና ለህዝብ ጠቃሚ የሆኑ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን ለህዝቡ በማቅረብ በውድድሩ ተቀባይነትን ለማግኘትና ለጋራ ተጠቃሚነት መረጋገጥ መስራት ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ ይጠበቃል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ነው።
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል
Mar 6, 2026 134
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዝግጅት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ገለጹ። 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ በተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የመራጮች ምዝገባ ከነገ ጀምሮ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመራጮች ምዝገባ ለአንድ ወር እንደሚካሄድ ገልጸው፤ ምዝገባው በዲጂታል እና በማንዋል መልኩ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል። ከፕሌይ ስቶርና አፕ ስቶር "ምርጫዬ" የተሰኘውን መተግበሪያ አውርደው በስልካቸው መመዝገብ የሚችሉ ዜጎች በራሳቸው መመዝገብ እንደሚችሉም ጠቁመዋል። በአካል ምርጫ ጣቢያዎች የሚመዘገቡ መራጮችን ለማስተናገድም ቦርዱ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ታብሌቶችን ማሰራጨቱን አብራርተዋል። ከ3 ጂ በላይ ኢንተርኔት ተደራሽነት ባለባቸው አካበቢዎች የመራጮች ምዝገባው በዲጂታል እንደሚደረግ ጠቁመው፤ ለዚህም ቦርዱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን ማስመዝገባቸውን አክለዋል። ከዚህ ውስጥ 2ሺህ 198 ዕጩዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመዘገቡ ሲሆን 8 ሺህ 736 ለክልል ምክር ቤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ እንዳሉት 73 በግል በዕጩነት የቀረቡ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 69ኙ ወንድ 4ቱ ደግሞ ሴት ዕጩዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቦርዱ ፓርቲዎች የሚወዳደሩበትን ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብንም ፓርቲዎች እንዲፈርሙ መደረጉን ከቅድመ ዝግጅት ስራዎች መካከል መሆኑን አብራርተዋል።
ለመራጭነት የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህርዳርና የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ
Mar 6, 2026 84
ባህር ዳር/ጀረር፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህር ዳር ከተማ እና በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሔደው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ ተአማኒና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። መራጮች መዝገባም ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀመር ቦርዱ ያሳወቀ ሲሆን ኢዜአም በባህርዳር ከተማና እና በሶማሌ ክልል ጀረር ዞን ከተሞች ነዋሪዎች መምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ ያላቸውን ዝግጁነት በማስመልከት አነጋግሯል። በባህር ዳር ከተማ ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎቹ መካከል አቶ ሰይፈአርዕድ ሙሏለም እንደገለጹት ዘንድሮ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይመራኛል፤ ያስተዳድረኛል ብለው ያመኑበትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ እየተዘጋጁ ነው። እንደሀገር ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች በንቃት በመሳተፍ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መብታቸውን ማረጋገጣቸውን አስታውሰዋል። ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝግባም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በምርጫው እለት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ፣ ሀገረ መንግስቱን ለማጽናትና ልማትን ለማፋጠን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊና ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ነዋሪዋ፣ ህብረተሰቡ በምርጫው ለመሳተፍ በወቅቱ በመመዝገብ የመራጭነት ካርድ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ማረጋገጥና የፈለግነውን ፓርቲ መምረጥ የምንችለው የምርጫ ካርድ በወቅቱ ስንይዝ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ አማረ ጌጡ ናቸው። በተመሳሳይ በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎችም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የዞኑ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ሃይብ ሳላህ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ቀኑን እየተጠባበቁ ናቸው። በተለይ የሴቶችን እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። "በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይሆነኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቺያለሁ" ያሉት ደግሞ አቶ አብዱላሂ ዊል መሀሙድ ናቸው። በተለይ ለአገር አድገት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥና ተግቶ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ምርጫቸው መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም በነገው እለት የመራጮች ምዝገባ ካርድ ለመውስድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ከአጠቃላይ የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17 ሺህ ያህሉ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
ማህበራዊ
በኦሮሚያ ክልል የመንገድ ተደራሽነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተፋጠኑ ነው
Mar 7, 2026 40
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የመንገድ ተደራሽነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት መጠናከራቸውን የክልሉ መንገድና ሎጂስቲክስ ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር መሐመድ ኑራ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋትና የመንገድ አስተዳደርን ለማዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ተግባራት በቅንጅት እየተሠሩ ነው። በበጀት ዓመቱ በክልል ደረጃ የሚገነቡ በርካታ መንገዶች መኖራቸውንና ከእነዚህ መካከልም ያደሩ 21 መንገዶችና አዳዲስ ደግሞ 4፣ በአጠቃላይ 25 የመንገድ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ በመንግሥት በጀት፣ ኅብረተሰቡን በማሳተፍና በሌሎች የገቢ ምንጮች የመንገድ ግንባታና ጥገና እንዲሁም የድልድዮችና የፓርኪንግ ፕሮጀክቶች ግንባታ በስፋት መከናወኑን ገልጸዋል። በገጠር የመንገድ ልማት መርሃ ግብር በዞኖችና ወረዳዎች 503 ኪሎ ሜትር ለመገንባት ታቅዶ እስካሁን 75 ኪሎ ሜትር ግንባታው መጠናቀቁን አንስተዋል። በተጨማሪም በዚህ ዓመት 21 ትላልቅ ድልድዮች በክልል ደረጃ ለመገንባት ታቅዶ አፈጻጸማቸው 56 በመቶ መድረሱንም ተናግረዋል። ከመንገድ ግንባታ ሥራው ጎን ለጎን በአሰላ፣ ፊቼ፣ ጊምቢ፣ ነቀምቴና ቡሌ ሆራ ከተሞች ዘመናዊ መነኸሪያ ግንባታ እየተፋጠነ ነው ብለዋል። የመንገድ አስተዳደርን በማዘመን የአገልግሎት ጊዜውን ለማራዘም የመንገዶቹ ጥገናና እንክብካቤ ላይ ትኩረት መደረጉንም አክለዋል።
ሙዚየሙ ለሀገር ግንባታ ዝግጁ የሆነ ትውልድ ለመቅረጽ ትልቅ ፋይዳ አለው
Mar 7, 2026 51
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሰራዊት ሙዚየም የዘመናት የጀግንነት ጉዞ የሚዘክር ሕያው አሻራ ከመሆን ባለፈ ለሀገር ግንባታ ዝግጁ የሆነ ትውልድ ለመቅረጽ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የመከላከያ ሙዚየምና ቅርስ ጥናት አስተዳደር ዳይሬክተር ሜጄር ጄኔራል ጥሩዬ አሰፌ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በታሪኳ በፈተናዎች ጸንታ የቆመችው በማይበገረው የሠራዊታችን ተጋድሎ ነው -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የሀገሪቱን ታሪካዊ ወታደራዊ ጉዞና የጀግንነት አሻራዎችን የያዘውን የኢትዮጵያ ሰራዊት ሙዚየም ጎብኝተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጉብኝቱን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ሠራዊት ሙዚየም የጀግንነታችን ማኅደር፣ የልዕልናችን ምስክር ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪኳ በፈተናዎች ጸንታ የቆመችው በማይበገረው የሠራዊታችን ተጋድሎ እንደሆነም ተናግረዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጃንሜዳ አካባቢ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሠራዊት ሙዝየም መጎብኘታቸውን ገልጸው፤ በሙዝየሙ የዘመናት የጀግንነት ጉዞ የሚመሰክሩ ህያው አሻራዎችን መመልከታቸውን ጠቁመዋል። የመከላከያ ሙዚየምና ቅርስ ጥናት አስተዳደር ዳይሬክተር ሜጄር ጄኔራል ጥሩዬ አሰፌ እንደገለጹት፤ ሙዚየሙ ከአክሱም ዘመነ መንግስት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ያሉ የኢትዮጵያን ወታደራዊ ታሪኮች እና ቅርሶች በዝርዝር ሰንዶ የያዘ ነው። ከለውጡ በኋላ መንግስት ለታሪክና ለቅርስ ባሳየው ቁርጠኝነት ሙዚየሙ በዘመናዊ መልኩ እንደ አዲስ መገንባቱን ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሠራዊት ጀግንነት በተግባር የሚታይበት ነው ብለዋል፡፡ ጀግኖች አባቶቻችን በዓድዋ ጦርነት ወቅት የተጠቀሙባቸው መሣሪያዎችን ጨምሮ የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር የተከፈሉ መስዋዕትነቶችን የሚያሳዩ ተጨባጭ ማስረጃዎች እንደሚገኙበትም አስረድተዋል። የሙዚየሙ መገንባት ትውልዱ የሀገሩን ታሪክ በቀላሉ እንዲረዳ ያስችለዋል ሲሉም ገልጸዋል፡፡ ሙዚየሙ ሠራዊቱን በጀግንነት የሚያነሳሳ ከመሆኑ ባለፈ ወቅቱ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት በመክፈል ለሀገር ግንባታ ዝግጁ የሆነ ትውልድ ለመቅረጽ ያስችላል ብለዋል። ሙዚየሙ ኢትዮጵያ በታሪኳ ሁሉ ሉዓላዊነቷን በተግባር ማረጋገጧን በግልጽ የሚያሳይ እንደሆነም ጨምረው አንስተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በቦታው ተገኝተው መጎብኘታቸውም ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረባቸው ጠቁመው ለሙዚየሙ ታሪካዊ ፋይዳ እውቅና የሚሰጥና ለዘርፉ የተሰጠውን ልዩ ትኩረት የሚያረጋግጥ መሆኑንም ተናግረዋል።
የወጣቶችን ስብዕና በሚያንጹ ተግባራት ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይገባል - ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)
Mar 7, 2026 53
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፡- የነገዋን ሀገር የሚመሩ ወጣቶችን ስብዕና ማነፅ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ ኢንቨስት ማድረግ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። በዘመናዊ መልክ ዕድሳት የተደረገለት፣ ልዩ ልዩ ቁሳቁስ የተሟላለት እና አዲስ የተገነባ የስፖርት መጫወቻ ሜዳን ያካተተው የአጋሮ ከተማ የወጣቶች ስብዕና ማዕከል አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ሚኒስትሯ የማዕከሉ አገልግሎት ማስጀመሪያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራችን ብልጽግና የዛሬውም ሆነ የወደፊት ሀገር መሪ ወጣቶችን ስብዕና ማነፅ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ ኢንቨስት ማድረግ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል። ማዕከሉ የመንግሥት፣ የማኅበረሰቡና የአጋር አካላት የተቀናጀ ጥረት ብሎም የመደመር ውጤት ነው ማለታቸውን ሚኒስቴሩ ለኢዜአ የላከው መረጃ አመላክቷል። በከተማውና አካባቢው የሚገኙ ወጣቶች በማዕከሉ በአግባቡ እንዲገለገሉና አስፈላጊውን እንክብካቤ እንዲያደርጉም አሳስበዋል። ወጣቶች በመልካም ስብዕና ታንፀው፣ ዕውቀታቸው ዳብሮ፣ እጃቸው በክኅሎትና በሙያ ተፍታትቶ ከአካባቢያቸው ባለፈ ለሀገር ብልፅግና ጉልህ አስተዋፅዖ እንዲያበረክቱም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ማዕከሉ የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት፣ የአይ ሲ ቲ፣ የሥልጠና አዳራሾች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ ካፍቴሪያና የምክር አገልግሎትን መስጠት በሚያስችል መልኩ ከማዘመንና ከእድሳት በተጨማሪ በልዩ ልዩ ቁሳቁስ እንዲሟላ መደረጉንም አረጋግጠዋል። ሚኒስቴሩ በሌሎችም አካባቢዎች የሚገኙ ማዕከላትን ከማዘውተሪያነት ባለፈ ወደ ስብዕና ማበልፀጊያነት እንዲሸጋገሩ ብሎም የተሟላ፣ ዘመናዊና ሁለገብ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል በቅንጅት ይሠራል ብለዋል። የተባበሩት መንግሥታት የሥነ-ሕዝብ ፈንድ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ኮፊ ኩዋሜ በበኩላቸው፤ እያንዳንዱ ወጣት እምቅ ዐቅሙን የሚጠቀምበት ዓለም እውን ለማድረግ አስፈላጊውን የቴክኒክ፣ የማቴሪያልና የዐቅም ግንባታ ድጋፍ እናደርጋለን ነው ያሉት። Ethiopian News Agency
በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት ለመከላከል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በንቃት ሊሰሩ ይገባል
Mar 6, 2026 75
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃትን ለመከላከል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ በንቃት መስራት እንዳለባቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስገነዘበ። 5ኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት "ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላምና አካታች ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል መከፈቱ ይታወቃል። የዚሁ መርሃ ግብር አካል የሆነ የ'ኢምፓዚ ፎር ላይፍ ኢንተግሬትድ ዲቨሎፕመንት አሶሴሽን' (ኤሊዳ) (ELIDA) የተዘጋጀ በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት መከላከል ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ሶስት አላማዎችን ያነገበ ነው። እነዚህም ትብብር እና ቅንጅትን ማጠናከር፣ መልካም ተሞክሮዎችን መጋራት እና ለፖሊሲ የሚሆኑ ግብዓቶችን ማሰባሰብ መሆኑን ተናግረዋል። በሴቶች ላይ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት መከላከል ላይ ያደረገው ውይይትም ከዓላማዎቹ አንጻር ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በሀገር ግንባታና በዜጎች ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርገው፣ ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት በንቃትና መስራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል። ጠንካራ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕድሎችንና ፈተናዎችን ቀድሞ በመለየት ዘመኑን የዋጀ ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸውን አንስተዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን ለመከላከል የኅብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግና ጉዳዩን የጋራ አጀንዳ በማድረግ በንቃት መሥራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ተረፈ ዴጌቲ በበኩላቸው፣በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃትን በህግ እና በፖሊሲ ማእቀፎች መከላከል እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህም የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎም ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የ'ኢምፓዚ ፎር ላይፍ ኢንተግሬትድ ዲቨሎፕመንት አሶሴሽን' (ኤሊዳ) ዋና ዳይሬክተር ዚነት ይመር ማህበሩ ላለፉት 18 ዓመታት በሴቶች ትምህርት፣ በሰላም ግንባታ እና በኢኮኖሚ ማብቃት ላይ ሰፊ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሰው ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት እየጨመረ መምጣቱ የሴቶችን ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ተሳትፎ እየገደበው መሆኑን ጠቁመዋል። ይህንን ችግር ለመከላከልም የሁሉንም አካላት ትብብር፣ ቅንጅት እና አሳታፊ ምህዳር መፍጠር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። ማህበሩም ይህንን የጥቃት አይነት በዘላቂነት ለመፍታት በተለያዩ አካባቢዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮጀክት አመራር፣ ትብብር እና የሀብት ማሰባሰብ ቡድን መሪ ሳምሶን ኒሻን ችግሩን ለመከላከል የሴቶች የፖሊሲ ክለሳ ተደርጎ በመጨረሻ ረቂቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ጉዳቱን ለመከላከል ጠንካራ መሰረት እንደሚጥል ገልጸው በስትራቴጂዎችም የተቀመጡ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ከዲጂታል እውቀት አንጻር ውስንነቶች መኖራቸውን አንስተው ተጠቂዎችም ሰፊ የግንዛቤ ክፍተት እንዳለባቸው ገልጸዋል። የሴት መብት ተሟጋች እና በሥርዓተ-ፆታ እኩልነት እንዲሁም በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ የምትሰራው ሰላማዊት ተዘራ ህጎች ቢኖሩም ሰፊ የአፈጻጸም ክፍተት መኖሩን አንስታለች። በቴክኖሎጂ እውቀት ረገድ ሰፊ ክፍተት መኖሩን ገልፀው፣ ችግሩን ለመቅረፍ ተከታታይነት ያላቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰጠት እንዳለባቸውም ተናግራለች። በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት ከፍተኛ የስነ ልቦና ጫናን የሚፈጥር መሆኑን የገለጸችው ደግሞ የሥርዓተ-ፆታ እኩልነት እና የማህበራዊ አካታችነት ጥናት ባለሙያ ሀና ለማ ናት። ድርጊቱ ዝቅ ተደርጎ ሳይታይ ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገልፃለች።
ኢኮኖሚ
የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎች እየተዘረጉ ነው
Mar 7, 2026 41
አዳማ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በዘላቂነት ለመጠበቅና የዘርፉን አሰራር ለማዘመን የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎችን እየዘረጋ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ገለጸ። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና የኢትዮጵያን የንግድ ምህዳር ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታላቅ ዕድል ነው ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የረቂቅ ደንቡን ይዘት በባለድርሻ አካላት ግብዓት ለማዳበር ያለመ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል። የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በህግ ለመደገፍ አዋጅ ቁጥር 1376/2018 ወጥቶ ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጓል። ይህም የሀገሪቱን የእንስሳትና የእንስሳት ውጤቶች የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳለጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው አሰራር ለመዘርጋት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። አምባሳደር ድሪባ አክለውም፤ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና ምርቱን የሚረከቡ ሀገራት የሚቀበሏቸው የህግ ማዕቀፎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል። አሁን ላይ በእፅዋትና በእንስሳት ዘርፎች አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ስታንዳርዶች ፀድቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የህግ ማዕቀፎቹ የዘርፉ ኢንዱስትሪዎች፣ በተለይም የስጋ አምራቾች ፍላጎትን መሰረት ያደረጉና ከዓለም አቀፍ አሰራር ጋር የተናበቡ እንዲሆኑ ታስቦ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የባለሥልጣኑ የሬጉላቶሪ ዘርፍ ዳይሬክተር ሃሚድ ጀማል (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባለፉት ሰባት ወራት የእንስሳት ምርት ለማምረት ፈቃድ የተሰጣቸውን ተቋማት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የአሰራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውን ገልጸዋል። ምርት ወደ ውጭ ከመላኩ በፊት ከማምረቻው ጀምሮ ጥራትና ደህንነቱ መጠበቅ እንዳለበት ያመለከቱት ዳይሬክተሩ፤ ምርት በቁምም ሆነ ታርዶ ለተጠቃሚው ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ እንዲላክ ተቋሙ ከግብርና ሚኒስቴርና ከባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የባለሥልጣኑ የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አያሌው ሹመት በበኩላቸው፤ የህግ ማዕቀፎቹ የኤክስፖርት ዘርፉን ማነቆዎች የሚቀርፉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ይህም የቁም እንስሳት፣ ስጋ፣ ዶሮ፣ እንቁላል፣ ዓሣ፣ ወተትና የማር ምርቶችን የቁጥጥር አሰራር የሚያዘምን መሆኑን ጠቅሰዋል። በህግ ማዕቀፎቹ ዝግጅት ወቅት የዓለም ንግድ ድርጅትን ጨምሮ የናሚቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ቦትስዋና፣ እንግሊዝና የብራዚል ምርጥ ተሞክሮዎች እንዲካተቱ አድርገናል ሲሉም ገልጸዋል። የህግ ማዕቀፎቹ ተግባራዊ መሆን ለሀገሪቱ የወጭ ንግድ ውጤታማነት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረውም ተመላክቷል።
በክልሉ በቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል
Mar 7, 2026 29
ጂንካ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 ዓ/ም ግማሽ ዓመት የስራ አፈፃፀሙን በጂንካ ከተማ እየገመገመ ነው። የቢሮው ኃላፊ ኤካል ነትር በወቅቱ እንደገለፁት፤ ቢሮው በቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት መለወጥ የሚያስችሉ የተቀናጁ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ በተለይም ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ ቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የመስኖ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ የአየር ንብረት ተፅእኖውን በመቋቋም የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ከሚተገበሩ ፕሮጀክቶች መካከል የመስኖ ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም በቆላማ አካባቢዎች ሰፋፊ የመስኖ አውታሮችን በመገንባት አርብቶ አደሩ በግብርና ልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን መደረጉን ገልጸዋል። በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራትም የአንድ ከፍተኛ እና የሁለት መካከለኛ ግድቦች የግንባታ ስራ መጀመሩን ጠቁመው፥ ወደ 8 የሚሆኑ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ደግሞ በተያዘው ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በተያዘው ዓመት ከሚጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መካከል የአርጎባ፣ ብላቴኤታ፣ ማርቃላሾ፣ ሎማቴ እና ሳላ የተሰኙ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ በአካባቢው በመስኖ የማልማት ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ አርብቶ አደሩና ከፊል አርብቶ አደሩን ያማከለ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ማስፋፋት የሚያስችል የጥናትና ዲዛይን ስራ እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል። ከመስኖ ልማት ባሻገር በግጦሽ ሳር ከለላ፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ፣ በንፁህ መጠጥ ውሃና በመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በእንስሳት ግብይት ማዕከላት ግንባታና በሌሎች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ቦሼ ቦምቤ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቢሮው በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ገልፀዋል። አርብቶና ከፊል አርብቶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በዘላቂነት ኑሮውን ለማሻሻል የተጀመረው የመስኖ ልማት እንዲጠናከር የክልሉ መንግስት በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡ በተለይ በግንባታ ላይ ያሉ የመስኖ ፕሮጀክቶች በአጭር ጊዜ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የተቀናጀ ርብርብ እንደሚደረግም ተናግረዋል። የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አብረሃም አታ በበኩላቸው፤ በዞኑ ቆላማ አካባቢዎች የተጀመሩ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች የከፊል አርሶ አደሩን ምርታማነት በማሻሻል በግብርና ልማት ተጠቃሚነቱ እንዲያድግ አድርጓል ብለዋል። የመስኖ ልማት መተግበር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ዓመቱን ሙሉ ለማልማት አቅም በመፈጠሩ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንዳስቻለም ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለቀጣናው ልማትና ሰላም መረጋገጥ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው
Mar 7, 2026 77
ሮቤ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን የሚያስተሳስሩ ግዙፍ የልማት ስራዎችን በማካሄድ ለቀጣናው ሰላም መረጋገጥ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር በሃሳብ ልዩነታችን ውስጥ የማንደራደርበት ቀይ መስመራችን ነው - የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ብሔራዊ ጥቅምን ያስከበረ ለአፍሪካ ቀንድ እና አጎራባች ሀገራት ትብብር፣ የጋራ ብልፅግና፣ ሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰላምና የልማት አቅም በመሆን ረገድ ያለችበትን ሁኔታ በማስመልከት ኢዜአ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንን አነጋግሯል። አስተያየታቸውን የሰጡ ምሁራንና ተመራማሪዎች እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ከማስከበር ባለፈ ለቀጣናው ብልፅግና የጋራ ተጠቃሚነት መርህ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን አመልክተዋል። በዩኒቨርሲቲው የጂኦግራፊና አካባቢ ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ ፈዬ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ የሰላምና የልማት አቅም እየሆነች መምጣቷን ተናግረዋል። በተለይ የአፍሪካ ቀንድ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ለንግድ እንቅስቃሴ ምቹ መሆኑን ተናግረዋል። ቀጣናው ጥቂት የማይባሉ አካላት ፍላጎት ያለበት መሆኑንና ኢትዮጵያም ብሔራዊ ጥቅሟን በሚያስጠብቅ መልኩ ከሀገራት ጋር በትብብር እየሰራች መሆኑ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመተባበር ቀጣናዊ ትስስርን የማጠናከር ጽኑ አቋሟን በተግባር እየገለጠች መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የስነ ዜጋና ሥነ ምግባር ትምህርት ክፍል መምህርና የቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር ጉተማ አደም ናቸው። ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በማከናወን ከራሷ አልፎ ለአካባቢው አገራት የጋራ ልማትና ተጠቃሚነት እየሰራች መሆኑን አመልክተዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ ለህዝቧ ፍላጎትና ተጠቃሚነት ይበጃሉ ብላ የምትወስዳቸው የተለያዩ እርምጃዎች ከሷ አልፎ ለቀጣናው ልማትና ሰላም መረጋገጥ የሚጠቅሙ በመሆናቸው የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣ እያስቻላት ስለመሆኑም አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በብሪክስ ባለ ብዙ ወገን የትብብር መድረክ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከራሷ አልፎ የአፍሪካን ድምጽ እያሰማች መሆኑን ያብራሩት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንትና ኢኮኖሚክስ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር ሁሳ አሎ ናቸው። ከዚህ አንፃር የኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ የልማት ጥረት በቀጣናውም ይሁን በአህጉሩ የስኬት መንገድ ውስጥ ትልቅ ድርሻ አለው ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በተለይም በኃይል፣ በትራንስፖርት እና በሌሎች መሠረተ ልማቶች ለማስተሳሰርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እያደረገች ያለው ጥረት በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ እንደሚያጠናክርም አክለዋል።
የጅግጅጋ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋት ነው
Mar 7, 2026 81
ጅግጅጋ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ የጅግጅጋ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ምቹ የመኖሪያ አካባቢ ከማድረግ ባለፈ ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋት መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ። በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በክልሎችም እየተስፋፋ ስማርት፣ ምቹና ዘመናዊ ከተሞችን እውን የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል። ፕሮጀክቱ የከተማችን ብቻ ሳይሆን የሀገራችን ኩራትና ገጽታን የሚቀይር ስኬት ነው -ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለአኗኗርና ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበሩ ከተሞች በኮሪደር ልማት የብስክሌትና እግረኛ መንገዶችን ጨምሮ የመዝናኛ እና የመጫወቻ ስፍራዎችን በማካተት እየተሰሩ ይገኛሉ። በዚህ የልማት እቅድ ተጠቃሚ ከሆኑ ከተሞች መካከል በምስራቅ ኢትዮጵያ በንግድ እንቅስቃሴዋ የምትጠቀሰው ጂግጂጋ ከተማ አንዷ ነች። የጂግጂጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ታሪካዊ ይዘቷ ሳይለቅ፣ ዘመናዊነትን ከባህላዊ እሴቶች ጋር በማሰናሰል የከተማዋን ውበትና መልካም ገጽታ መግለጥ አስችሏል። በዚህም የከተማዋን የንግድ እንቅስቃሴ ይበልጥ ለማሳለጥና የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያስቻለ ዘመን ተሻጋሪ የልማት አሻራ መሆኑን ብዙዎች ይናገራሉ። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ አህመድ ቡራሌ ፋራህ፤ የኮሪደር ልማቱ በተከናወነባቸው የከተማዋ አካባቢዎች ለንግድም ይሁን ለመዝናኛ ምቹ ሆነው አግኝተናቸዋል ብለዋል። የእግረኛ፣የብስክሌት እና የተሽከርካሪዎች መንገድ ተለይተው መገንባታቸውን አንስተው በዚህም የትራፊክ አደጋን ለመከላከልና ለሰዎች ነፃ እንቅስቃሴ መልካም እድል ፈጥሯል ሲሉ ተናግረዋል። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሱልጣን አብዲ ከሊፍ፤ የጂግጂጋ ከተማ ለውጥ አስደናቂ እና አስደማሚ መሆኑን ገልጸው መንግስትን አመስግነዋል። ለአካባቢው ከተሞች የልማት ተምሳሌት በመሆን የንግድና የኢንቨስትመንት ልማትን እና የቱሪዝም እንቅስቃሴን ለማሳለጥ የሚያስችል የከተማ ልማት እየተከናወነ ስለመሆኑ አንስተዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ተሌህ ደይብ፤ በጂግጂጋ ከተማ የኮሪደር ልማት በተጨማሪ በከተማዋና አካባቢው የሰይድ መሀመድ አብድሌ ሀሰን ሚሞሪያል ፓርክ እና ሌሎችም የመስህብ ስፍራዎች በአጭር ጊዜ በላቀ ጥራት ተገንብተው መጠናቀቃቸው አስደንቆናል ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጣው ለውጥ በተለይም ለሶማሌ ክልል ልዩ እድል የፈጠረ መሆኑንም አንስተዋል። በከተማዋ የተሠሩና እየተሠሩ ያሉ መዝናኛ ፓርኮች ከተለያዩ አከባቢዎች የሚመጡ እንግዶች እና የከተማዋ ነዋሪዎች ለመዝናናት ምቹ እድል የሚፈጥሩ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል፤ ለዚህም ድጋፍና ትብብራችን አይለይም ሲሉ አረጋግጠዋል። በከተማዋ የተጠናቀቁ እና በሂደት ላይ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ትልቅ ተስፋ የሰነቅንባቸው ናቸው ያሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ መሀመድ ኢብራሂም ናቸው። በከተማ ልማቱ ለዘመናዊ አኗኗር እና ለጉብኝት ምቹ አካባቢ ከማድረግም ባለፈ ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ታስተናግዳለች
Mar 7, 2026 37
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ(ASMIS) ልታስተናግድ ነው። ጉባኤውን የሚያዘጋጁት ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ (POA) እና ኤ.ጂ.ኤ ቴክ (AGA-Tech) ኢንተርፕራይዝ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። ጉባኤው እ.አ.አ ግንቦት 7 እና 8 ቀን 2026 በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል። የመጀመሪያ የሆነው ይህ ጉባኤ የአፍሪካ ተፅዕኖ ፈጣሪ ድምፆችን ከመገናኛ ብዙኅን ድርጅቶች፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የግሉ ዘርፍ መሪዎች ጋር የሚያገናኝ ታሪካዊ የጋራ መድረክ መሆኑ ተገልጿል። ''ተፅዕኖ ለተሻለች አፍሪካ'' በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው ጉባኤው የዲጂታል ተሳትፎ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂና ኃላፊነት ላይ ምክክር የሚደረግበት ወሳኝ መድረክ እንደሚሆንም ይጠበቃል። የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ አስተባባሪ በረከት ሲሳይ እንደገለጹት፤ ጉባኤው ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ባለው ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የአፍሪካን የዲጂታል ገጽታና ይዘት ፈጠራ ላይ ትኩረት ያደርጋል ብለዋል። በጉባኤ የቴክኖሎጂ ሥነ-ምኅዳር ፈጠራ፣ የአፍሪካ ታሪክና መፃኢ ተስፋዎች ላይ ጥራት ያላቸው የይዘት ሥራዎችን ለማስተጋባት አቅም የሚፈጠር አህጉራዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሁነቱ በአፍሪካ ሀገራትና በዓለም ዙሪያ የሚሰሩ ከ200 በላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበራዊ ሚዲያ ግለሰቦች ተሰባስበው የሚመክሩበት መሆኑንም ተናግረዋል። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦቹ በዘላቂ ልማት፣ ዲጂታል አስተዳደርና የይዘት ፈጠራ አቅምን የሚያጎለብቱ የምክክርና የትውውቅ መርሃ ግብሮች እንደሚያካሄዱ አብራርተዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት ልምድና ተሞክሮ የሚለዋወጡበት፣ የአፍሪካን ዕድገት በዲጂታል ሥርዓት መግለጥ የሚያስችል እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጠሪዎችን ከትላልቅ የንግድ ድርጅቶች ጋር የሚያገናኝ መድረክ መሆኑንም አንስተዋል። የኤ.ጂ.ኤ ቴክ (AGA-Tech) ኢንተርፕራይዝ አስተባባሪ ባዩሽ ማሞ በበኩላቸው፤ ጉባኤው እያደገ በመጣው የዲጂታል ዓለም የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር ትብብርና ተወዳዳሪነት ለማጎልበት አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሚካሄደው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ይፋዊ ምዝገባ በቅርቡ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። በዚህም የይዘት ፈጣሪዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችና ባለድርሻ አካላት ጉባኤውን የሚመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት በ www.asmis.org ድረ-ገጽን መከታተል እንደሚችሉ ገልጸዋል። የአህጉሪቱን ዲጂታል መጻኢ የፈጠራ አቅምና እጣ ፈንታ በተሻለ ይዘት ለመቅረጽ ጉባአው ወሳኝ መሆኑን ተናግረው ታላላቅ የንግድ ተቋማትና ድርጅቶችም ለጉባኤው ስኬታማነት በአጋርነት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረምን ታስተናግዳለች
Mar 7, 2026 76
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ስምንተኛው የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረም ሚያዚያ 18 እና 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ያዘጋጀው ፎረም “ አጀንዳ 2030 እና አጀንዳ 2063ን በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ዲጂታል ኢኖሼሽን ውጤታማ ማድረግ” በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል። ፎረሙ የአፍሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ኢኖቬተሮች እና የልማት አጋሮች በአንድ መድረክ ያገናኛል። ባለድርሻ አካላቱ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያለውን ሚና አስመልክቶ በፎረሙ ይመክራሉ። መድረኩ የአፍሪካ የኢኖቬሽን አጀንዳን የበለጠ ለማራመድ የሚያስችል ቁልፍ ማዕቀፍ ሆኖ እንደሚያገለግልም ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በመንግስት፣ በአካዳሚክ ማህበረሰቡ፣ በኢንዱስትሪ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ውይይት ይደረጋል። ፎረሙ አፍሪካ በዘላቂ ልማት ግቦች የደረሰችበትን የአፈጻጸም ደረጃ ይገመግማል። ውሃ እና ንጽህና፣ ተመጣጣኝ እና ንጹህ ኢነርጂ፣ ኢንዱስትሪ እና መሰረተ ልማት፣ ዘላቂ ከተሞችና የልማት አጋርነት ጨምሮ የተለያዩ የዘላቂ ልማት ግቦችን የተመለከተ ውይይት ይካሄዳል። የውይይቱ ተሳታፊዎች ኢኖቬሽን ተኮር መፍትሄዎች እና ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር የሚያስችሉ የተግባር እርምጃዎች ላይ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። በፎረሙ ላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ ከፍተኛ አዎንታዊ ለውጥ ያመጡ ቴክኖሎጂዎች፣ ጀማሪ የስራ ፈጠራዎች (Startups)፣ የምርምር ኢኒሼቲቮች እና የኢኖቬሽን ማዕከላት ስራዎች ለእይታ ይቀርባሉ። ኹነቱ የእውቀት ሽግግርን ለማሳለጥ፣ በዩኒቨርሲቲዎች እና ምርምር ተቋማት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር እንዲሁም በአፍሪካ ያለውን የቴክኖሎጂ ሽግግር የመደገፍ አላማ አለው። በፎረሙ ላይ የአፍሪካ ሀገራት መንግስታት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አመራሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረም ውጤቶች በአዲስ አበባ የሚካሄደውን 12ኛው የአፍሪካ ቀጣናዊ የዘላቂ ልማት ፎረም የሚደግፉ መሆናቸው ተመላክቷል። 12ኛው የአፍሪካ ቀጣናዊ የዘላቂ ልማት ፎረም ከሚያዚያ 20 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
ኢንስቲትዩቱ የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ ምርምሮችን እያከናወነ ነው
Mar 6, 2026 149
አዳማ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ የጥናትና ምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት እንደገለጹት፤ ተቋሙ በኦሮሞ ባህል፣ እሴት፣ ስነ-ጥበብ፣ ታሪክ፣ ቋንቋና እድገት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። ወጣቶች መልካም ስብዕናን ተላብሰው ለሀገር ልማት እና እድገት እንዲተጉ የባለድርሻ አካላት ሚና ሊጠናከር ይገባል ይህንንም ውጤታማ ለማድረግ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ከሚገኙ ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ከቱሪዝም ኮሚሽን፣ ከባህል ጥናት ማዕከል እንዲሁም ከወጣቶችና ስፖርት ቢሮዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ እስካሁን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ከ70 በላይ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ከእነዚህም መካከል በታሪክ፣ በቋንቋና በባህል ላይ ያተኮሩ ከ30 በላይ መጻሕፍት ታትመው ለማህበረሰቡ ተደራሽ ሆነዋል ብለዋል። እነዚህ ስራዎች በተለይም የወጣቶችን የማንበብ ባህል ለማጠናከርና ሁለንተናዊ ስብዕናቸው እንዲገነባ ለማስቻል ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም አመልክተዋል። የጥናት ውጤቶቹንና የመጻሕፍት ዝግጅቱን አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች፣ ስራው በትውልዱ ላይ የሚታየውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት እንደሚረዳ ገልጸዋል። ወጣት ስራጅ አህመድ እንደገለጸው፣ ንባብ ወጣቶች ስለ ማህበረሰቡ ስብዕናና ባህል እንዲያውቁ ያደርጋል። የገዳ ስርዓት መሰረታችንና ማንነታችን ነው ያለው ወጣት ስራጅ፣ ስለ ስርዓቱና ስለ ኦሮሞ እሴቶች በቂ እውቀት ለማግኘት የንባብ ባህላችንን ማጎልበት ይገባናል ብሏል። ተተኪው ትውልድ ስራን ከመናቅ ወጥቶ በልማት ስራዎች ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለበትም ነው የገለጸው።
የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ “ንዋይ” የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያን ይፋ አደረገ
Mar 5, 2026 141
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (ESX) የካፒታል ገበያን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል “ንዋይ” የተሰኘ የሞባይል ግብይት መተግበሪያ ዛሬ ይፋ አድርጓል። መተግበሪያው በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ማንኛውም ግለሰብ በሞባይል ስልኩ በመጠቀም በአክሲዮን እና በዕዳ ሰነዶች ግብይት ላይ በቀጥታ እንዲሳተፍ እድል የሚሰጥ ነው። የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማኤል (ዶ/ር) በመተግበሪያው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ እንደተናገሩት፤ "ንዋይ" ገበያውን በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እጅ ላይ ተደራሽ ያደርገዋል። መተግበሪያው ባለሀብቶች በማንኛውም ጊዜና ቦታ ሆነው በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ውስጥ በቀጥታ እንዲሳተፉ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው የሰነድ ግዢና ሽያጭ ትዕዛዞችን በስልክ ማስተላለፍና መፈጸም እንሚያስችልም ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተህልቁ በበኩላቸው በርካታ ሀገራት ወደዚህ ዓይነት የቴክኖሎጂ ሥርዓት ለመድረስ ረጅም ጊዜ እንደወሰደባቸው አስታውሰዋል። ኢትዮጵያ ግን ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ በመማር በአጭር ጊዜ ውስጥ ዘመናዊ የገበያ ሥርዓት መገንባቷን ገልጸዋል። ይህ ሥርዓት ልዩ የሚያደርገው አካታችነቱ ነው ያሉት ዳይሬክተሯ በሁሉም የሀገሪቱ ጫፍ ያሉ ዜጎች የኢንቨስትመንት አካውንት በመክፈት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ መንግስት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው ግልጽና ተገማች የሆኑ ህጎች መውጣታቸው ለዚህ ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥራ አስፈጸሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)፣ ገበያው ሁሉም ዜጋ በአቅሙ ልክ የሚሳተፍበት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። እንደ ቴሌ ብር እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) መተግበሪያዎች ያስመዘገቡት ስኬት ለ"ንዋይ" ውጤታማነት እንደ ማሳያ እንደሚጠቀስም ገልጸዋል። መተግበሪያውን በአሁኑ ወቅት በአንድሮይድ (Android) እና በአይኦኤስ (iOS) ስልኮች ላይ ለመጫን ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የካፒታል ገበያ ባለቤት ማድረግ ግብን ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል።
ስፖርት
የኤፍኤ ካፕ ባለ ብዙ ክብሩ አርሰናል ከማንስፊልድ ታውን ጋር ይጫወታል
Mar 7, 2026 68
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፡- በእንግሊዝ ኤፍኤ ካፕ አምስተኛ ዙር መርሐ-ግብር የሁለተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ከ15 ላይ በፊልድ ሚል ስታዲየም ማንስፊልድ ታውን ከአርሰናል ይጫወታሉ። በአራተኛው ዙር ማንስፊልድ በርንሌይን፣ አርሰናል ዊጋን አትሌቲክን አሸንፈዋል። ሁለቱ ክለቦች በኤፍኤ ካፑ ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም እ.አ.አ በ1929 በአራተኛ ዙር ተገናኝተው አርሰናል 2 ለ 0 አሸንፏል። ከ97 ዓመታት በኋላ በድጋሚ በኤፍኤ ካፕ ውድድር ይገናኛሉ። ማንስፊልድ ታውን በውድድሩ ትልቁ ውጤቱ እ.አ.አ 1968/59 ሩብ ፍጻሜ የገባበት ነው። አርሰናል 14 ጊዜ የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን በማንሳት ስኬታማው ክለብ ነው። መድፈኞቹ ለመጨረሻ ጊዜ ውድድሩን ያሸነፉት እ.አ.አ በ2020 ነበር። ማንስፊልድ ታውን በእንግሊዝ እግር ኳስ ሊግ ሶስተኛ እርከን (ሊግ ዋን) የሚጫወት ቡድን ነው። አርሰናል የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን በ64 ነጥብ እየመራ ነው። ጨዋታውን አርሰናል የማሸነፍ ከፍተኛ ግምት ወስዷል። በሌሎች መርሐ-ግብሮች ሬክስሃም ከቼልሲ ምሽት 2 ሰዓት ከ45፣ ኒውካስትል ዩናይትድ ከማንችስተር ሲቲ ምሽት አምስት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ትናንት ማምሻውን በተደረገ የኤፍኤ ካፕ የመጀመሪያ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሊቨርፑል ዎልቭስን 3 ለ 1 በማሸነፍ ለሩብ ፍጻሜ አልፏል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሃዋሳ ከተማ ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር ይጫወታል
Mar 7, 2026 47
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ከተማ ከሃዋሳ ከተማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። አዲስ አበባ ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በሁለቱ አሸንፎ በስድስቱ በ12 ተሸንፎ በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ ስምንት ግቦችን ሲያስቆጥር 32 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በስምንት ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ በበኩሉ በ16 ጨዋታዎች ዘጠኝ ጊዜ ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 28 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 11 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ሃዋሳ ከተማ በ32 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ ይጫወታሉ። በሌላኛው መርሐ-ግብር ባህርዳር ከተማ ከሸገር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ባህርዳር ከተማ ከሸገር ከተማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ባህር ዳር ከተማ በሊጉ 16 ጨዋታዎች አድርጎ ሶስት ጊዜ ድል ሲቀናው በ12ቱ ተሸንፏል። በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይቷል። ስምንት ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ 22 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ10 ነጥብ 12ተኛ ደረጃን ይዟል። በውድድር ዓመቱ ካከናወናቸው 16 ጨዋታዎች መካከል 10ሩን ያሸነፈው ሸገር ከተማ በአምስቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ አንድ ጨዋታ ነጥብ ጥሏል። በ16ቱ ጨዋታዎች 26 ግቦችን ሲያስቆጥር 18 ጎሎችን አስተናግዷል። ሸገር ከተማ በ31 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። አርባምንጭ ከተማ ከአዳማ ከተማ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በሊጉ ሁለት ጨዋታዎችን ብቻ ያሸነፈው አርባምንጭ ከተማ በዘጠኝ ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። አዳማ ከተማ በ16 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በ16ኛ ሳምንት አርባምንጭ ከተማ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አዳማ ከተማ በሲዳማ ቡና ሽንፈት አስተናግደዋል። ሁለቱ ቡድኖች ከሽንፈቱ አገግመው ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይፋለማሉ።
ሊቨርፑል በኤፍኤ ካፕ ሩብ ፍጻሜ የገባ የመጀመሪያው ቡድን ሆኗል
Mar 7, 2026 56
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ኤፍኤ ካፕ የአምስተኛ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታ ሊቨርፑል ዎልቭስን 3 ለ 1 አሸንፏል። በሞልኒው ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አንዲ ሮበርትሰን፣ መሐመድ ሳላህ እና ከርቲስ ጆንስ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሂ-ቻን ዋንግ ለዎልቭስ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ላይ ሊቨርፑል ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል። ውጤቱን ተከትሎ ሊቨርፑል ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለ የመጀመሪያ ክለብ ሆኗል። የዎልቭስ የኤፍኤ ካፕ ጉዞ አምስተኛ ዙር ላይ ተገቷል። ሁለቱ ቡድኖች ከቀናት በፊት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 29ኛ ሳምንት ተገናኝተው ዎልቭስ 2 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የእንግሊዝ ኤፍኤ ካፕ አምስተኛ ዙር እስከ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
አካባቢ ጥበቃ
የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከስጋት መታደግ የሚያስችል የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ ይሰራል
Mar 7, 2026 57
አርባ ምንጭ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የስምጥ ሸለቆ ተፋሰስ የሆኑ የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከስጋት ለመታደግ የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ እንደሚሰራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተባባሪነት የአባያና ጫሞ ሀይቆች የሚያስከትሉትን ተጽእኖ መቀነስ የሚያስችል የባለድርሻ አካላት ውይይት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት የአባያና ጫሞ ሀይቆችን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሉ ከፀጋነት ወደ ስጋትነት እየተቀየሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይ በጋሞ፣ በጋርዱላ፣ በኮንሶና በቡርጂ ዞኖች የሚገኙ አርሶ አደሮችን ማሳ እንዲሁም በተለያዩ መሠረተ ልማቶች ላይ አደጋ እያስከተሉ ይገኛሉ ብለዋል። በመሆኑም ሐይቆቹን ከስጋት ለመታደግ የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ እንደሚጠናከር ገልጸዋል፡፡ ተፋሰሶቹ የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር፣ የፍራፍሬ፣ የብዝሃ ህይወት የቱሪዝምና የቀጣናዊ ልማት ማሳለጫዎች መሆናቸውን ጠቅሰው ከስጋት ወደ ሀብት ምንጭነት ለመቀየር የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በውሃው ዘርፍ የረጅም ጊዜ ልምድ ያለው አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉን ችግሮች ለመቅረፍ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው የክልሉ መንግስት የበኩሉን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። የማዕድን ሚኒስትርና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በበኩላቸው የአባያና ጫሞ ሃይቆችን በዘላቂነት መጠቀም ለሃገር ሁለንተናዊ ብልጽግና ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በአርባ ምንጭና አካባቢው መልከ ብዙ ፀጋዎች መኖራቸውን ጠቅሰው የሀይቆቹን ትሩፋት ለማጉላት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በአግባቡ ሊከናወን እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተገኙ ጥናቶች መሠረት የተፋሰሶቹን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ፕሮግራሞች፣ ስትራቴጂዎችና ፕሮጀክቶች ተቀርጸው መተግበር እንዳለባቸውም አመልክተዋል። የአባያና ጫሞ ሀይቆች የውሃ መጠን መጨመር፣ የተፋሰሱ ወንዞች ሙላትና ደለል ከፍተኛ አካባቢያዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎችን እያስከተሉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አብደላ ከማል(ዶ/ር) ናቸው። የአባያና ጫሞ እንዲሁም ሌሎች ተፋሰሶች በተቀናጀ ሁኔታ ካልተመሩ ተጽዕኖው ከሀይቆቹ ዳርቻ አልፎ ሰፊ ቦታዎችን ሊያዳርስ እንደሚችል በጥናት መረጋገጡንም ጠቅሰዋል። ዩኒቨርሲቲው በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች የሚከሰቱ ተግዳሮቶችን በሳይንሳዊ መንገድ ለመከላከል የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የስራ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎችም እየተሳተፉ ነው።
የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ተምሳሌታዊ ተግባር ነው
Mar 7, 2026 48
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አርአያ የሚሆን ስራ እያከናወነች እንደምትገኝ የዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን ገለጹ። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባትና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን ማምረት፣ አረንጓዴ አሻራ፣ የስንዴ ምርታማነት፣ የኢትዮጵያ የማዳበሪያ እና የጤናማ አፈር ፍኖተ ካርታ፣ አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን የመስኖ ስራዎች ማስፋትና የተራቆቱ መሬቶችን በአካባቢ ጥበቃ ስራ ወደ ነባር ይዞታቸው መመለስ ከተከናወኑ ተግባር መካከል ይጠቀሳሉ። የዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እየገነባች ያለችው አቅም የሚደነቅ መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ስኬታማ ስራዎችን እያከናወነች እንደሚገኝ ጠቅሰው እንደ አረንጓዴ አሻራ ባሉ ኢኒሼቲቮች የቀጣናው ሀገራት ተጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የዘርፉ ስኬቶች ለማስፋት መንግስት፣ ቀጣናዊ ተቋማት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይበልጥ ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸውም አመልክተዋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በቀጣናው የሚገኙ ሀገራት በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ያላቸውን አቅም የበለጠ ማጠናከር እንደሚኖርባቸውም ነው ባለሙያው የገለጹት። በዚህ ረገድ የዓለም ባንክ ከመንግስታት ጋር የግሉ ዘርፍ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ያለውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለማሳደግና በተለይም ለወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኢኖቬሽን፣ ዲጂታል መፍትሄዎች፣ ዘላቂ የኢነርጂ አጠቃቀም እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑንም ነው ያነሱት። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የዓለም የግብርና ፋይናንስ ከፍተኛ ለውጥ ማሳየቱን ገልጸው ሀገራት ፋይናንስ በዘላቂነት የሚያመጡ አጋርነቶችን መፍጠር እንዳለባቸው መክረዋል። ለዚህ ተቋማት ትስስራቸውን ማጠናከር፣ አማራጭ ፋይናንስ መፈለግ፣ እሴት መጨመር ትኩረት መስጠት እና ለጋራ ግብ በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ ነው
Mar 6, 2026 111
ጋምቤላ ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች በቀጣዮቹ ሶስት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ መሆኑን በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋምቤላ ክልል ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል በኢንስቲትዩቱ የጋምቤላ ክልል የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋሁን ዓለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ወይና ደጋማ አካባቢ በቀጣይ ወራት የሚኖረው የበልግ ዝናብ ለእርሻ ስራ ተስማሚ ነው። በክልሉ ወይና ደጋማ የአየር ፀባይ ያለው የማጃንግ ዞን በቀጣዩቹ ሶስት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለእርሻ ስራና ለእንስሳት ግጦሽ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር የአየር ትንበያ መረጃ ያመለክታል ብለዋል። በተለይም በዞኑ ቀድመው ለሚዘሩ የሰብል ዓይነቶችና ለመኸር እርሻ ስራ ዝግጅት በቂ የዝናብ ስርጭት እንደሚኖር መተንበዩን አመላክተዋል ። በሌላ በኩል ደግሞ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች ጠንከር ያለ የሙቀት መጠን እንደሚኖር የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጸዋል። በመሆኑም የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር የውሃ መጠን መቀነስ ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ ውሃን በአግባቡ መጠቀም እንዳለበት ምክር ሃሳብ ሰጥተዋል። እንዲሁም ከሙቀቱ መጨመር ጋር ተያይዞ በሰዎች ላይ የቆዳ ሽፍታ ሊከሰት ስለሚችል ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል
Mar 5, 2026 105
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አስከፊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ገለጸ። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ተፈፃሚነት ያላት ቁርጠኝነት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንዳስቻላት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ተቋማዊ ልማት አማካሪ መንሱር ደሴ ገልጸዋል። ከየካቲት 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የአውደ ጥናት የምክክር መድረክ ተጠናቋል። በአውደ ጥናቱ ማጠናቀቂያ ላይ የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የአፍሪካ አስተባባሪ ጆንኪ ቴኑ፤ የአካባቢና የሥነ-ምኅዳር ደኅነንት ለማስጠበቅ ትብብርን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል። አውደ ጥናቱም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ተግባራዊ የተደረጉ መርሃ ግብሮችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ስኬታማ የልምድ ልውውጥና ግብዓት እንደተገኘበት ገልጸዋል። በፖሊሲዎችና የትኩረት መስኮች የተደረገው ውይይትም የዕውቀት ሽግግር የተደረገበት መሆኑን ተናግረዋል። ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የመንግሥታቱን ድርጅት የአየር ንብረት ስምምነት መነሻ በማድረግ ለተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ እያቀረበ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሀገራትም የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አስከፊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚያግዝ አረጋግጠዋል። በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ተቋማዊ ልማት አማካሪ መንሱር ደሴ በበኩላቸው፤ በአውደ ጥናቱ ከ14 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 150 ሙያተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ትግበራ ያላት ቁርጠኝነት በልማት አቅጣጫዎቿ ላይ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን አስረድተዋል። በአውደ ጥናቱም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም በተደረገ ድጋፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት መቅረባቸውን ተናግረዋል። ከሀምሌ ወር ጀምሮ ለአራት ዓመታት የሚተገበረው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም መርሃ ግብርም ከኢትዮጵያ የልማት አቅጣጫዎች ጋር ተጣጥመው እንደሚተገበሩ አንስተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በሰላምና ደኅንነት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Mar 5, 2026 101
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢጋድ የሰላም እና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ውይይቱን ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁን (ዶ/ር) በመወከል ነው። ውይይቱ ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም፣ ደኅንነት እና መረጋጋት ላይ ያላቸውን የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው። ሁለቱ ወገኖች የጋራ የተግባር ምላሽ ለመስጠት እና ስትራቴጂካዊ ትብብራቸውን ለማጎልበት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የመንግሥታቱ ድርጅትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ ይገባል
Mar 4, 2026 199
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ እንደሚገባ ተገለጸ። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከጃፓን ኤምባሲ ጋር በመሆን የተባበሩት መንግሥታት ሪፎርም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል። የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ ቢሆኑም በተቋማዊ አወቃቀር ሥርዓት ላይ አፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ያገለሉ ናቸው። የአማኒ አፍሪካ ዳይሬክተር ሰለሞን አየለ ደርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት መዋቅር የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃ ሊወስድ ይገባል። በተቋማቱ የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥም ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ተከታታይ ሥራ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትና ከሌሎች ሀገራት ጋር ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን የዓለምአቀፍ ተቋማት ፍትሐዊ ውክልና ማስከበር የሚስችል መዋቅራዊ የሪፎርም እርምጃ እንዲወሰድ መስራት ይገባል ብለዋል። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በአፍሪካ ሕብረትና የአፍሪካ ዳያስፖራ ጉዳዮች ላይ በጥናትና ምርምር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የጋና አምባሳደር ሮበርት አፍሪይ(ዶ/ር)፤ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ያቀረበችው ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ችላ በመባሉ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ የሌላት ብቸኛ አህጉር አድርጓታል ብለዋል። ለዚህም የመንግስታቱ ድርጅት አፍሪካ በተሸከመችው የጸጥታው ምክር ቤት የሥራ ጫና ልክ ውክልና የሚያስገኛትን የሪፎርም እምርጃ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። በአፍሪካ ሕብረት የጃፓን ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኖቦሩ ሴኪጉቺ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በመንግስታቱ የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ላይ ፍትሐዊ ውክልና ሊሰጣት ይገባል ብለዋል። ጃፓንም አፍሪካ በመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የሚኖራትን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። ጃፓንና የጂ-4 አባል ሀገራት የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡም አስታውቀዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2024 በጸደቀው "የወደፊት ስምምነት" ላይ የጸጥታው ምክር ቤት መዋቅራዊ የማሻሻያ እርምጃ ለመወሰድ የተቀመጠው አቅጣጫ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቀጣናዊ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 1, 2026 167
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ እያሳደረ ባለው ከፍተኛ ተጽእኖ ምክንያት የቀጣናው የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እና የዜጎች የኑሮ መሰረት አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብ ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል።
የኢጋድ እና ተመድ ትብብር ለቀጣናዊ ሰላም
Feb 26, 2026 195
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ያላቸውን የጋራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የኢጋድ የደቡብ ሱዳን ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሙሳ ጃማ አሊ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። ልዩ ልዑኮቹ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት በተለይም በደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት የአምስት አባል ሀገራት ኮሚቴ (AU C5) እና ኢጋድ ያደረጉት የጋራ ጉባኤ የተገኙ ውጤቶች ላይም መክረዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ሰላም፣ መረጋጋት እና ቀጣናዊ ትብብር እውን እንዲሆን ያላቸውን ቅንጅት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 212
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 262
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 270
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 711
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 295
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 399
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1132
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1119
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3616
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2414
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8210
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6694
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 410
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 387
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።