ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ እና የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ታሪካዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Jun 8, 2026 87
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) በመካከላቸው ያለውን ለረጅም ጊዜ የቆየ አጋርነት በአዳዲስ የትብብር መስኮች ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ። በአፍሪካ ህብረት እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ለምለም ፍስሃ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኮሚሽኑ ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ዛሬ አቅርበዋል። በዚሁ ወቅትም አምባሳደሯ እና ዋና ጸሐፊው በሁለትዮሽ እና በጋራ ፍላጎቶች ዙሪያ ተወያይተዋል። ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው፣ በኢትዮጵያ እና በኮሚሽኑ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነትና አጋርነት አንስተዋል። ይህንን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው አዳዲስ የትብብር መስኮች ዙሪያ የሀሳብ ልውውጥ ማድረጋቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። አምባሳደር ለምለም ፍስሃ ባለፈው ሳምንት ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የሹመት ደብዳቤያቸውን ማቅረባቸው የሚታወስ ነው።
የአፍሪካ እና አውሮፓ የጤና እና ሰብአዊ ፈተናዎች ምላሽ አጋርነት
Jun 8, 2026 116
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ ህብረት ከአፍሪካ ጋር ያለውን የጤና እና ሰብአዊ ፈተናዎችን የመከላከል አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኝነቱን ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የአውሮፓ ህብረት የእኩልነት፣ ዝግጁነት እና የቀውስ አስተዳደር ኮሚሽነር ሃጃ ላህቢብን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። የአውሮፓ ህብረት ለዓለም አቀፍ የጤና ፈተናዎች እያደረገ ያለውን ድጋፍ ያነሱት ሚኒስትሩ፣ በተለይም የኢቦላ ወረርሽኝን ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው የጋራ እንቅስቃሴ ህብረቱ ላሳየው አጋርነት ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል። ህብረቱ የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (Africa CDC) ያደረገው ድጋፍ፣ ሊከሰቱ የሚችሉ ዓለም አቀፍ የጤና ስጋቶችን በጋራ ለመከላከል ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለኮሚሽነሯ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ኮሚሽነር ሃጃ ላህቢብ በበኩላቸው፤ የአውሮፓ ህብረት ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የጋራ መፍትሄ የሚሹ የጤና እና የሰብአዊ ፈተናዎችን በትብብር ለመፍታት ህብረቱ ዝግጁ እንደሆነ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕውቀትን ለትውልድ የሚያሻግር ምኅዳር እየገነባ ነው
Jun 8, 2026 142
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕውቀትን ለትውልድ የሚያሻግር ምኅዳር እየገነባ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገለጹ። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ40 በላይ የመጽሐፍት አከፋፋዮች፣ አሳታሚዎችና የመጽሕፍት መደብሮች የሚሳተፉበትን 18ኛውን ዓመታዊ የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ በስድስት ኪሎ ግቢ ይፋ አድርጓል። ከሰኔ 1 ቀን እስከ ሰኔ 7/2018 ዓ.ም የሚቆየው ዓውደ ርዕይም በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች የሚያተኩሩ ነባርና አዳዲስ መጽሐፍት ለአንባቢያን በቅናሽ ዋጋ ቀርበዋል፤ አዳዲስ መጽሐፍትም ይመረቃሉ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት፤ የዩኒቨርሲቲው ፕሬስ ከ50 ዓመታት በላይ በርካታ መጽሐፍትን ሲያሳትምና ተደራሽ ሲያደርግ ቆይቷል ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ጉዞም የፕሬስ አቅምን በማጎልበና የዘመን ገበያን በመጠቀም የመጽሐፍትን ተደራሽነት የሚያሰፉ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም አርቲፊሻል ኢንተለጀንስና ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕውቀትን ለትውልድ የማሻገርና ተቋሙ ከሌሎች መሰል ተቋማት ጋር ያለውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እንደሚሠራ ገልጸዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ደርብ አዶ (ዶ/ር)፤ ዓውደ ርዕዩ የመጽሐፍት ሽያጭ፣ የደራሲያን የልምድ ልውውጥ፣ ውይይትና የፕሬስ ሕትመቶች ምርቃት ይካሄድበታል ብለዋል። በቀጣይም የዩኒቨርሲቲውን ፕሬስ ዓለም አቀፍ ተደራሽነት የሚያሰፉ ተግባራትን የበለጠ ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። በዓውደ ርዕዩ ከተሳተፉት መካከል የክብሩ መጽሐፍት መደብር ተወካይ ሜሮን ይልማ፤ ዓውደ ርዕዩ የንባብ ባህል እንዲሁም የተጠቃሚዎችን ቁጥር ለማሳደግ መነቃቃት የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ሕፃናት በጨዋታ መልክ የሚያስተምሩ መጫወቻዎችን ይዘው የቀረቡት የፊት በር ቶይስ ተወካይ ሚካኤል ግርማ በበኩላቸው፤ ዓውደ ርዕዩ ምርታቸውን ለማስተዋወቅ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ መምህር ሶንግ ሩዶንግና ዩሊያን ዡ ዩሉ በበኩላቸው፤ ዓውደ ርዕዩ ተማሪዎች መጽሐፍት እንዲያገኙና የንባብ ባህል እንዲያዳብሩ የሚያስችል ነው ብለዋል። ዓውደ ርዕዩው በርከት ያሉ መጽሐፍት የቀረቡበት በመሆኑ አንባቢያን የሚፈልጉትን እንዲያገኙ ያስችላል ያሉት ደግሞ መህዲ አብዱረዛቅና ጅሎ ከሚ ናቸው። በዓውደ ርዕዩ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አምባሳደር ቶፊቅ አብዱላሂ (ዶ/ር)፤ ዓውደ ርዕዩ የንባብ ባህልን በማዳበር ወጣቶችና ታዳጊዎች ዕውቀት ማሳደግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። በቀጣይም ዜጎች የንባብ ባህላቸውን በማጎልበት በዕውቀትና ምክንያታዊነት የተመሰረተ ዕሳቤን ማበልፀግ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።
የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 8, 2026 273
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፤ ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው ብለዋል። 9ኛው አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ ዛሬ መጀመሩንም አስታውቀዋል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ለህዝቡ ቃል በተገባው መሰረትም የዛሬውን ጨምሮ ዘጠኝ ማዕከላትን ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ጠቁመዋል። ይህ አሰራር የአገልግሎት እንግልትን፣ ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅረፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝብን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ነው ያብራሩት። ህዝቡ ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል ለማድረግ የታቀደውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ከንቲባዋ ገልጸዋል። በየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ላደረጉት አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
ምክር ቤቱ የጉምሩክ ማሻሻያ እና የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጆችን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል
Jun 8, 2026 294
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ 24ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ያካሂዳል። ምክር ቤቱ በዚሁ መደበኛ ስብሰባው የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ይመክራል። በጉዳዩ ላይ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያዘጋጀውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮም አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጅ ላይ ያዘጋጀውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ እንደሚያጸድቅም ምክር ቤቱ አመልክቷል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ እና የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ታሪካዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Jun 8, 2026 87
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) በመካከላቸው ያለውን ለረጅም ጊዜ የቆየ አጋርነት በአዳዲስ የትብብር መስኮች ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ። በአፍሪካ ህብረት እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ለምለም ፍስሃ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኮሚሽኑ ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ዛሬ አቅርበዋል። በዚሁ ወቅትም አምባሳደሯ እና ዋና ጸሐፊው በሁለትዮሽ እና በጋራ ፍላጎቶች ዙሪያ ተወያይተዋል። ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው፣ በኢትዮጵያ እና በኮሚሽኑ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነትና አጋርነት አንስተዋል። ይህንን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው አዳዲስ የትብብር መስኮች ዙሪያ የሀሳብ ልውውጥ ማድረጋቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። አምባሳደር ለምለም ፍስሃ ባለፈው ሳምንት ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የሹመት ደብዳቤያቸውን ማቅረባቸው የሚታወስ ነው።
ምክር ቤቱ የጉምሩክ ማሻሻያ እና የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጆችን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል
Jun 8, 2026 294
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ 24ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ያካሂዳል። ምክር ቤቱ በዚሁ መደበኛ ስብሰባው የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ይመክራል። በጉዳዩ ላይ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያዘጋጀውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮም አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጅ ላይ ያዘጋጀውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ እንደሚያጸድቅም ምክር ቤቱ አመልክቷል።
ምርጫ ቦርድ ነገ በልዩ የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ድምፅ የመስጠት ሂደት እንደሚከናወን ገለጸ
Jun 8, 2026 295
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና በወታደራዊ ካምፖች በሚገኙ ልዩ ጣቢያዎች ነገ በልዩ ሁኔታ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት እንደሚከናወን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት ማስፈጸሙን አውስቷል። በአሁን ሰዓት ቦርዱ ከምርጫ ክልል ጽህፈት ቤት ወደ ቦርዱ ማዕከል በመምጣት ላይ ያሉ ውጤቶችን የማረጋገጥ፣ የኦዲት ግኝት ያለባቸውን ውጤቶች የመመርመር እንዲሁም የተረጋገጡ ውጤቶችን ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ሥራ ላይ እንደሚገኝም አመልክቷል። በተጨማሪም በፖለቲካ ፓርቲዎችና በግል ዕጩዎች የቀረቡ አቤቱታዎችን በሕግ ባለሙያ ጉባዔ አማካኝነት የማደራጀትና ምሥክር የመሥማት ሥራ እያከናወነ ነው። በቀጣይም በተጠቀሰው ሂደት ያለፉ ውጤቶች ለቦርድ ውሣኔ በማቅረብ እና በማፀደቅ በሕጉ መሠረት ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግም ቦርዱ አስታውቋል። ቦርዱ “በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 17” በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም የካምፑ ነዋሪዎችን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ እንዲሣተፉ በመራጭነት መመዝገቡ ይታወቃል። በመሆኑም በካምፖቹ በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ድምፅ የመስጠት ሂደት ነገ እንደሚከናወን ቦርዱ በመረጃው አመልክቷል።
በዞኑ የሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በሙሉ አቅም ለማከናወን ምቹ ሁኔታ ፈጥሮልናል -ነዋሪዎች
Jun 8, 2026 206
አምቦ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በሙሉ አቅም ለማከናወን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው የዞኑ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ምዕራብ ሸዋ ዞን በተለያየ መልኩ ለጸጥታ ችግር ተጋልጠው ከቆዩ የኦሮሚያ ክልል ዞኖች መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል። የአካባቢውን ሰላም አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እንዳሉት በአካባቢያቸው አስተማማኝ ሰላም መስፈኑ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴያቸውን በተሻለ ለማከናወን ችለዋል፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡ ነዋሪዎች መካከል አቶ ግርማ ሲያ፤ ከዚህ ቀደም በአካባቢያቸው አጋጥሞ የነበረው የጸጥታ ችግር መፈታቱ በልማት ሥራዎች ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ከዚህም ባለፈ ለብዙ ዓመታት ሲያነሷቸው የነበሩ የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ ሀይልና የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ለመሆን መቻላቸውን ጠቅሰዋል። አሁን የአካባቢያችን ሰላም አስተማማኝ በመሆኑ የልማት ጥያቄዎች እየተመለሱልን ነው፤ እኛም አካባቢያችንን ተደራጅተን እየጠበቅን ነው ብለዋል። ሌላዋ ነዋሪ ወይዘሮ መብራት አስማማው በበኩላቸው፤ በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም እየጠበቅን የዕለት ተዕለት የልማት ስራዎቻችንን ያለምንም ስጋት እያከናወንን እንገኛለን ብለዋል። በቀጣይ ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ አንጻር ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር የሚያደርጉትን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል፡፡ በአካባቢያችን አሁን ያለው ሰላም አስተማማኝ በመሆኑ በልማት ስራዎች ላይ የምናድረገው ተሳትፎ አድጓል ብለዋል። በዞኑ የቶኬ ኩታዬ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አለሙ ሂርኮ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ህዝቡ ከመንግስት የጸጥታ መዋቅር ጋር ተባብሮ በአንድነት በመስራቱ ዘላቂ ሰላም ማምጣት ተችሏል፡፡ በዚህም በወረዳው በሁሉም የገጠርና የከተማ አካባቢዎች ነዋሪዎች መደበኛ የልማት ሥራዎችን ያለምንም የጸጥታ ስጋት እያከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የወረዳው ነዋሪ ያለምንም የሰላም ስጋት ወጥቶ የዕለት ተዕለት መደበኛ ሥራውን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ የህብረተሰቡን ጥያቄ የሚመልሱ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታም እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዞኑ ሰላምን ለማስፈን በተሰሩ ሥራዎች በአሁኑ ወቅት ዘላቂ ሰላም መስፈኑን የተናገሩት ደግሞ የምዕራብ ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳደሪ አቶ አበበ ጨመዳ ናቸው። በዞኑ ባለፉት አምስት ዓመታት በአንዳንድ ወረዳዎች ላይ የሰላም እጦት አጋጥሞ እንደነበር አስታውሰው፤ ህብረተሰቡ በየደረጃው ካለ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ ሰላም ሰፍኗል ብለዋል። በዚህም ቀደም ሲል ተስተጓጉለው የነበሩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እየሆኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያን ታሪክና ልዕልና በሚመጥን መልኩ እየሰራ ነው - ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል
Jun 8, 2026 303
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያን ታሪክና ልዕልና በሚመጥን እንዲሁም ዘመኑን በዋጀ መልኩ ተግባራዊ ስራዎች እየሰራ መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገለጹ፡፡ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ እንደገለጹት ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የሪፎርም ትግበራ ያካሄደው ተቋሙ አሁን ላይ ወንጀልን አስቀድሞ የመከላከል ጠንካራ ቁመናን ገንብቷል፡፡ ይህም ከተለዋዋጭ ሁኔታ እና ዲጂታሉ ዓለም ጋር እኩል እንዲጓዝ አድርጎታል ብለዋል፡፡ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያን ታሪክና ልዕልና በሚመጥን መልኩ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፤ በዓለም አቀፍና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን መከላከል ላይ ስኬታማ ስራ መስራቱን አንስተዋል። ተቋሙ በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር በተለያዩ አቅጣጫዎች መረባቸውን በመዘርጋት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን ከነመሪያቸው በመያዝ የፍርድ ሂደታቸውን እንዲከታተሉ ማድረጉንም አመልክተዋል። መሰል የወንጀል ድርጊት የሚከሰትበትን ቀጣና በመለየት ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ የብዙ ዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ በሚገኘው ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ በቁርጠኝነት የከወነው ስራ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት አድናቆት የተቸረው ሆኗል ብለዋል። በዚህም ተቋሙ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ወንጀሎች ቁጥጥር ላይ አይተኬ ሚናውን እየተወጣ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡ በዘርፉ ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር የተቋሙን ተጽዕኖ ከፍ ማድረግ ተችሏልም ነው ያሉት። የወንጀል ድርጊቶች ከጊዜ ወደጊዜ እየረቀቁ በቴክኖሎጂም እየላቁ ቢመጡም ፌደራል ፖሊስ በዛው ልክ አቅሙን በማጠናከር ዘመኑን በዋጀ መንገድ ተግባሩን መቀጠሉን ማረጋገጣቸውን የዘገበው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።
የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳለፈ
Jun 8, 2026 439
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ከተወያየ በኋላ ውሳኔዎችን አሳልፏል። ምክር ቤቱ በቀዳሚነት የተወያየው፣ የሀረሪ ብዙኃን መገናኛ ኤጀንሲን የሀረሪ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ በሚል ስያሜ እንደገና ለማቋቋም በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው። ይህም የተቋሙን ሥልጣንና ተግባራት የሕዝብ ብሮድካስት አገልግሎት ተቋማት በአሁኑ ወቅት ከደረሱበት የዕድገት ደረጃ ጋር ማጣጣም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ሲሆን፤ ተቋሙ በብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ ደረጃ ተደራጅቶ በብቃት፣ በጥራትና በውጤታማነት እንዲሠራ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። ካቢኔው በረቂቅ አዋጁ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በማከል፣ እንዲጸድቅ ለክልሉ ምክር ቤት መርቶታል። መስተዳድር ምክር ቤቱ በሁለተኛነት የተወያየበት አጀንዳ፣ የፍልሰት ጉዳዮች አስተባባሪ ምክር ቤትና የትብብር ጥምረትን ለማቋቋም በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ ያተኮረ ነበር። ደንቡ ከክልሉ ነባራዊ ሁኔታ በመነሳትና አግባብነት ያላቸውን አካላት ያቀፈ ክልላዊ የፍልሰት ጉዳዮች አስተባባሪ ምክር ቤትና የትብብር ጥምረትን በማቋቋም፤ በሰው የመነገድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር፣ እንዲሁም የወንጀል ድርጊቱን በሚፈጽሙ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን እንደሚያስችል ተመላክቷል። ከዚህ በተጨማሪም የሕብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያግዝ አደረጃጀት በመፍጠር፣ የዜጎችን ተጋላጭነት የሚቀንሱ ተግባራትን ለማከናወንና ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት እንደሚያግዝ ተገልጿል። የመስተዳድር ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል። ቀጥሎም ምክር ቤቱ የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን ሥርዓትን ለማሻሻል በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ ውይይት አድርጓል። ደንቡ ቀደም ሲል ተግባራዊ በተደረገው ክልላዊ የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ሥርዓት የተጀመሩ አበረታች ሥራዎችን ማሻሻልን ያለመ ሲሆን፤ በተበታተነ መልኩ ሲተገበር የቆየውን አሠራር በተቀናጀ ሁኔታ በሁሉም የክልሉ የአስተዳደር እርከኖች አስተሳስሮ ለመምራት፣ እንዲሁም በክልሉ ሕብረተሰብ መካከል ያለውን የእርስ በእርስ የመደጋገፍ ባሕል በማጠናከር ፍትሐዊ፣ ጥራትና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የታለመ ነው። ከዚህም በላይ በማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ሥርዓት ውስጥ ተሳታፊ የሆኑ አስፈጻሚ አካላትን ተግባርና ኃላፊነት በግልጽ በማስቀመጥ፣ የሀብት አሰባሰብ ሥርዓትንና ተጠያቂነት የሰፈነበት የፋይናንስ አጠቃቀምን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል። መስተዳድር ምክር ቤቱ በዚህ ረቂቅ ደንብ ላይም በሰፊው ከተወያየ በኋላ ሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል። የካቢኔው የማጠቃለያ አጀንዳ የነበረው፣ የቱሪዝም ኮሚሽን ለማቋቋም በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ የመከረበት ጉዳይ ነው። የሀረሪ ክልል በዩኔስኮ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ ሁለት ቅርሶችን ጨምሮ፣ የበርካታ ቁሳዊና መንፈሳዊ ቅርሶች ባለቤት ናት። የቱሪዝም ዘርፍ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያበረክተውን ድርሻ ለማሳደግ፣ በአዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማትና በኢኮ-ቱሪዝም ዘርፍ ውጤቶችን ለማስመዝገብ፣ ዘርፉን በተቀናጀና በባለቤትነት የሚመራ ተቋማዊ አደረጃጀት እንዲኖረው ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል። ለዚህም የቱሪዝም ዘርፉን በራሱ የሚመራ፣ ከበጀትና ከሰው ኃይል አስተዳደር አንጻር ተቋማዊ ነጻነት ያለው የቱሪዝም ኮሚሽን ማቋቋም የዘርፉን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተገልጿል። የመስተዳድር ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል።
የጠቅላላ ምርጫው ስኬት ኢትዮጵያዊያን ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ለዓለም ያስመሰከሩበት ነው
Jun 8, 2026 400
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ስኬት ኢትዮጵያዊያን ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ለዓለም በድጋሜ ያስመሰከሩበት ትልቅ ሀገራዊ ሁነት መሆኑን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ ገለጹ። የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተስተጋቡ አሉታዊ ዘገባና ስሁት ምኞቶችን ያመከነ ታሪካዊ ድል መሆኑን ተናግረዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ ውሎ፤የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎችም እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ ተካሂዶ ፍፃሜውን አግኝቷል። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ ለኢዜአ እንደገለጹት፥የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተስተጋቡ አሉታዊ ዘገባና ስሁት ምኞቶችን ያመከነ ታሪካዊ ድል ነው። በምርጫ ሂደቱም የኢትዮጵያ ህዝብ ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ በመምረጥ መንግሥትን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ መመስረት እንደሚችል በተግባር ማሳየቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ሥርዓትና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ለዓለም ማስመስከሩን ተናግረዋል። በውጭ ዓለማት ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎችም የዜጎች የምርጫ ንቁ ተሳትፎ የዴሞክራሲ ባህል እያበበ መምጣቱን እንዳስገነዘበ አንስተዋል። በተቃራኒው የኢትዮጵያን በጎነት የማይሹ ውስን አካላት ያስተጋቡት ከንቱ ጩኸት በኢትዮጵያዊያን የነቃ ተሳትፎ መምከኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ በውጭ ሀገራትና የዲሞክራሲ ልምምድ በጎለበተባቸው ሀገራት የሚኖሩ ዲያስፖራዎች ጥያቄ ጭምር እንደነበር አንስተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው የኢትዮጵያዊያን ንቁ ተሳትፎም የዲሞክራሲ ሥርዓት ባህል ግንባታና ልምምድን ዳያስፖራው ማህበረሰብ በአዎንታ እንደሚመለከተው ጠቅሰዋል። በምርጫው ተሳትፎ ህዝቡ ለሀገር ግንባታና ሁለንተናዊ ዕድገት ያለውን ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት ለዓለም ህዝብ በተግባር ማሳየቱን አብራርተዋል። በውጭ ዓለማት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የሀገራቸውን ብዝኅ የዕድገት ተስፋ በመመልከትና በመጎብኘት በተፈጠረው የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።
ከየትኛውም ታጣቂ ቡድን ጋር ግንኙነት የለኝም - ኦብነግ
Jun 8, 2026 699
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ) ፦ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ውድቅ አደረገ። ኦብነግ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለገባው የሰላም ስምምነት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነትም አረጋግጧል። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ፤ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ፈጽሞ እንደማይተባበር፣ ስለ ድርጅቱ ወቅታዊ የአመራር ለውጥ እና በትክክለኛ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ መደገፍ ስለሚያስፈልግበት ሁኔታ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል። ኦብነግ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡- የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን በጽኑ የሚቃወም ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለተፈረመው የሰላም ስምምነት ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋግጣል፤ የስምምነቱን ድንጋጌዎች በሙሉ ለማክበር እና ተግባራዊ ለማድረግ ያለውን ዝግጁነትም ያረጋግጣል። በተመሳሳይ ኦብነግ የኢትዮጵያ መንግሥት የገባውን ቃል እንዲያከብር እና የስምምነቱን ሙሉ አፈጻጸም በቅን ልቦና እንዲያረጋግጥ ይጠብቃል። በጥቅምት 21 ቀን 2018 በአስመራ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዛሬ በሶማሊ ክልል ለሚታየው ሰላምና መረጋጋት እንደ መሠረት ሆኖ አገልግሏል። ስምምነቱ ከተተገበረበት ጊዜ ጀምሮ ክልሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሰላማዊና የተረጋጉ ክልሎች አንዱ ለመሆን የበቃ ሲሆን፣ ይህም የስምምነቱን አስፈላጊነት እና ሁሉም ወገኖች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል። ኦብነግ የአስመራው የሰላም ስምምነት ለሶማሊ ክልልና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ጥቅም እንዳስገኘ ያምናል። ከዚህም በላይ ኦብነግ በታሪኩ ሲታገላቸው የነበሩ በርካታ ዓላማዎች እንዲሳኩ አወንታዊ አስተዋጽኦ አድርጓል። በመሆኑም ኦብነግ በሶማሊ ክልል የተገኘውን ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት ሊያናጋ የሚችል ማንኛውንም ድርጊት ወይም ባህሪ በጥብቅ ይቃወማል። እንዲሁም በሰላም ስምምነቱ አማካኝነት የግል ፍላጎታቸውን ማሳካት ያቃታቸው ጥቂት ግለሰቦች አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ በመሞከር የድርጅቱን ስም ያለፈቃድ መጠቀማቸውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ያደርጋል። ኦብነግ መሰል ጥረቶች የድርጅቱን መርሆዎች እንደማያንጸባርቁ ወይም የሶማሊ ክልልን እና የሕዝቡን ጥቅም እንደማያገለግሉ ያምናል። ይልቁንም እነዚህ ጥረቶች በክልሉ የተገኘውንና በብዙ ልፋት የመጣውን ሰላምና መረጋጋት ጥርጥር የሌለው አደጋ ላይ የሚጥሉ ሲሆን፣ ከክልሉ ውጪ የሆኑና ከሶማሊ ክልል ሕዝብ ሕጋዊ ምኞት ጋር የሚጋጩ አጀንዳዎችን የሚያራምዱ ናቸው። በተጨማሪም ኦብነግ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ መንግሥት ለመጣል ዓላማ ካላቸው ሌሎች ድርጅቶች ጋር ምንም ዓይነት ጥምረት እንዳልመሠረተ ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ግልጽ ማድረግ ይሻል። በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት በኃይል ለማስወገድ መታገል ወይም ብቸኛ ዓላማቸው የመንግሥትን ሥልጣን በትጥቅ መያዝ ከሆኑ ድርጅቶች ጋር መሳተፍ የኦብነግ ዓላማ ሆኖ አያውቅም። የኦብነግ ተልዕኮ ሁልጊዜም የሶማሊ ክልል ሕዝቦችን መብት፣ ጥቅም እና ምኞት ማስከበር ላይ ያተኮረ ነው። እነዚህን ዓላማዎች በውይይት እና በጋራ ስምምነት መርሆዎች ላይ በመመሥረት፣ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለማሳካት ቁርጠኛ ሆኖ ይቀጥላል። ስለሆነም ኦብነግ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በግጭት ውስጥ ከሚሳተፉ የታጠቁ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት፣ ትብብር ወይም ተሳትፎ እንደሌለው በድጋሚ ያረጋግጣል። ኦብነግ ለሰላማዊ ግንኙነቶች ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን፣ የሶማሌ ክልልን ሰላም፣ መረጋጋት እና የሕዝብ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም ድርጊቶች ውድቅ ያደርጋል። ኦብነግ አክሎም ከድርጅቱ ምንም ዓይነት ውክልና እና ፈቃድ ሳይኖራቸው በተናጠል በንቀሳቀሱት የቀድሞው የፓርቲው ሊቀመንበር በአቶ አብዲራህማን ማህዲ አማካኝነት የድርጅቱ ስም ያለአግባብ ጥቅም ላይ መዋሉን ያብራራል። አቶ አብዲራህማን ማህዲ በአሁኑ ወቅት በኦብነግ ፓርቲ ውስጥ ምንም ዓይነት የአመራር ቦታ የሌላቸው ሲሆን፣ ፓርቲውን፣ ፖሊሲዎቹን ወይም ዓላማዎቹን አይወክሉም። እ.አ.አ በሰኔ 2025 በጅጅጋ በተካሄደው የኦብነግ ጉባኤ ላይ አቶ አብዲራህማን ማህዲ ከሊቀመንበርነት ኃላፊነታቸው በይፋ የተነሱ ሲሆን፣ አቶ አብዲካሪም ሼክ ሙሴ የኦብነግ ፓርቲ አዲስ ሊቀመንበር ሆነው በሥርዓቱ ተመርጠዋል። በመሆኑም ከዚያ ቀን በኋላ በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የተወሰዱ ማናቸውም እርምጃዎች፣ የተላለፉ ውሳኔዎች ወይም የተሰጡ መግለጫዎች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ አቋም የማይወክሉ በመሆናቸው እንደ ግል አመለካከታቸውና ተግባራቸው ሊቆጠሩ ይገባል። የኦብነግ ፓርቲ @ONLFofficial በሚል የሚታወቀው የኤክስ (የቀድሞው ትዊተር) አካውንት የፓርቲው ይፋዊ አካውንት እንዳልሆነ መግለጽ ይወዳል። ይህ አካውንት በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የሚተዳደር የግል አካውንት ሲሆን፣ በዚህ አካውንት አማካኝነት የሚታተሙ ይዘቶች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ ፖሊሲዎች፣ አቋሞች ወይም መግለጫዎች አይወክሉም። ኦብነግ ሁሉም የሚመለከታቸው ወገኖች፣ ደጋፊዎች፣ የሚዲያ ድርጅቶች እና የሕዝብ አባላት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ስለ ፓርቲው አቋም እንዲሁም እንቅስቃሴዎች መረጃ ለማግኘት በይፋ በተፈቀዱ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ እንዲደገፉ ያሳስባል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ እና የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ታሪካዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Jun 8, 2026 87
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) በመካከላቸው ያለውን ለረጅም ጊዜ የቆየ አጋርነት በአዳዲስ የትብብር መስኮች ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ። በአፍሪካ ህብረት እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ለምለም ፍስሃ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኮሚሽኑ ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ዛሬ አቅርበዋል። በዚሁ ወቅትም አምባሳደሯ እና ዋና ጸሐፊው በሁለትዮሽ እና በጋራ ፍላጎቶች ዙሪያ ተወያይተዋል። ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው፣ በኢትዮጵያ እና በኮሚሽኑ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነትና አጋርነት አንስተዋል። ይህንን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው አዳዲስ የትብብር መስኮች ዙሪያ የሀሳብ ልውውጥ ማድረጋቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። አምባሳደር ለምለም ፍስሃ ባለፈው ሳምንት ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የሹመት ደብዳቤያቸውን ማቅረባቸው የሚታወስ ነው።
ምክር ቤቱ የጉምሩክ ማሻሻያ እና የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጆችን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል
Jun 8, 2026 294
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ 24ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ያካሂዳል። ምክር ቤቱ በዚሁ መደበኛ ስብሰባው የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ይመክራል። በጉዳዩ ላይ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያዘጋጀውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮም አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጅ ላይ ያዘጋጀውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ እንደሚያጸድቅም ምክር ቤቱ አመልክቷል።
ምርጫ ቦርድ ነገ በልዩ የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ድምፅ የመስጠት ሂደት እንደሚከናወን ገለጸ
Jun 8, 2026 295
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና በወታደራዊ ካምፖች በሚገኙ ልዩ ጣቢያዎች ነገ በልዩ ሁኔታ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት እንደሚከናወን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት ማስፈጸሙን አውስቷል። በአሁን ሰዓት ቦርዱ ከምርጫ ክልል ጽህፈት ቤት ወደ ቦርዱ ማዕከል በመምጣት ላይ ያሉ ውጤቶችን የማረጋገጥ፣ የኦዲት ግኝት ያለባቸውን ውጤቶች የመመርመር እንዲሁም የተረጋገጡ ውጤቶችን ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ሥራ ላይ እንደሚገኝም አመልክቷል። በተጨማሪም በፖለቲካ ፓርቲዎችና በግል ዕጩዎች የቀረቡ አቤቱታዎችን በሕግ ባለሙያ ጉባዔ አማካኝነት የማደራጀትና ምሥክር የመሥማት ሥራ እያከናወነ ነው። በቀጣይም በተጠቀሰው ሂደት ያለፉ ውጤቶች ለቦርድ ውሣኔ በማቅረብ እና በማፀደቅ በሕጉ መሠረት ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግም ቦርዱ አስታውቋል። ቦርዱ “በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 17” በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም የካምፑ ነዋሪዎችን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ እንዲሣተፉ በመራጭነት መመዝገቡ ይታወቃል። በመሆኑም በካምፖቹ በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ድምፅ የመስጠት ሂደት ነገ እንደሚከናወን ቦርዱ በመረጃው አመልክቷል።
በዞኑ የሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በሙሉ አቅም ለማከናወን ምቹ ሁኔታ ፈጥሮልናል -ነዋሪዎች
Jun 8, 2026 206
አምቦ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በሙሉ አቅም ለማከናወን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው የዞኑ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ምዕራብ ሸዋ ዞን በተለያየ መልኩ ለጸጥታ ችግር ተጋልጠው ከቆዩ የኦሮሚያ ክልል ዞኖች መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል። የአካባቢውን ሰላም አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እንዳሉት በአካባቢያቸው አስተማማኝ ሰላም መስፈኑ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴያቸውን በተሻለ ለማከናወን ችለዋል፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡ ነዋሪዎች መካከል አቶ ግርማ ሲያ፤ ከዚህ ቀደም በአካባቢያቸው አጋጥሞ የነበረው የጸጥታ ችግር መፈታቱ በልማት ሥራዎች ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ከዚህም ባለፈ ለብዙ ዓመታት ሲያነሷቸው የነበሩ የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ ሀይልና የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ለመሆን መቻላቸውን ጠቅሰዋል። አሁን የአካባቢያችን ሰላም አስተማማኝ በመሆኑ የልማት ጥያቄዎች እየተመለሱልን ነው፤ እኛም አካባቢያችንን ተደራጅተን እየጠበቅን ነው ብለዋል። ሌላዋ ነዋሪ ወይዘሮ መብራት አስማማው በበኩላቸው፤ በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም እየጠበቅን የዕለት ተዕለት የልማት ስራዎቻችንን ያለምንም ስጋት እያከናወንን እንገኛለን ብለዋል። በቀጣይ ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ አንጻር ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር የሚያደርጉትን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል፡፡ በአካባቢያችን አሁን ያለው ሰላም አስተማማኝ በመሆኑ በልማት ስራዎች ላይ የምናድረገው ተሳትፎ አድጓል ብለዋል። በዞኑ የቶኬ ኩታዬ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አለሙ ሂርኮ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ህዝቡ ከመንግስት የጸጥታ መዋቅር ጋር ተባብሮ በአንድነት በመስራቱ ዘላቂ ሰላም ማምጣት ተችሏል፡፡ በዚህም በወረዳው በሁሉም የገጠርና የከተማ አካባቢዎች ነዋሪዎች መደበኛ የልማት ሥራዎችን ያለምንም የጸጥታ ስጋት እያከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የወረዳው ነዋሪ ያለምንም የሰላም ስጋት ወጥቶ የዕለት ተዕለት መደበኛ ሥራውን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ የህብረተሰቡን ጥያቄ የሚመልሱ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታም እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዞኑ ሰላምን ለማስፈን በተሰሩ ሥራዎች በአሁኑ ወቅት ዘላቂ ሰላም መስፈኑን የተናገሩት ደግሞ የምዕራብ ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳደሪ አቶ አበበ ጨመዳ ናቸው። በዞኑ ባለፉት አምስት ዓመታት በአንዳንድ ወረዳዎች ላይ የሰላም እጦት አጋጥሞ እንደነበር አስታውሰው፤ ህብረተሰቡ በየደረጃው ካለ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ ሰላም ሰፍኗል ብለዋል። በዚህም ቀደም ሲል ተስተጓጉለው የነበሩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እየሆኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያን ታሪክና ልዕልና በሚመጥን መልኩ እየሰራ ነው - ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል
Jun 8, 2026 303
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያን ታሪክና ልዕልና በሚመጥን እንዲሁም ዘመኑን በዋጀ መልኩ ተግባራዊ ስራዎች እየሰራ መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገለጹ፡፡ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ እንደገለጹት ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የሪፎርም ትግበራ ያካሄደው ተቋሙ አሁን ላይ ወንጀልን አስቀድሞ የመከላከል ጠንካራ ቁመናን ገንብቷል፡፡ ይህም ከተለዋዋጭ ሁኔታ እና ዲጂታሉ ዓለም ጋር እኩል እንዲጓዝ አድርጎታል ብለዋል፡፡ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያን ታሪክና ልዕልና በሚመጥን መልኩ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፤ በዓለም አቀፍና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን መከላከል ላይ ስኬታማ ስራ መስራቱን አንስተዋል። ተቋሙ በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር በተለያዩ አቅጣጫዎች መረባቸውን በመዘርጋት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን ከነመሪያቸው በመያዝ የፍርድ ሂደታቸውን እንዲከታተሉ ማድረጉንም አመልክተዋል። መሰል የወንጀል ድርጊት የሚከሰትበትን ቀጣና በመለየት ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ የብዙ ዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ በሚገኘው ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ በቁርጠኝነት የከወነው ስራ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት አድናቆት የተቸረው ሆኗል ብለዋል። በዚህም ተቋሙ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ወንጀሎች ቁጥጥር ላይ አይተኬ ሚናውን እየተወጣ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡ በዘርፉ ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር የተቋሙን ተጽዕኖ ከፍ ማድረግ ተችሏልም ነው ያሉት። የወንጀል ድርጊቶች ከጊዜ ወደጊዜ እየረቀቁ በቴክኖሎጂም እየላቁ ቢመጡም ፌደራል ፖሊስ በዛው ልክ አቅሙን በማጠናከር ዘመኑን በዋጀ መንገድ ተግባሩን መቀጠሉን ማረጋገጣቸውን የዘገበው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።
የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳለፈ
Jun 8, 2026 439
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ከተወያየ በኋላ ውሳኔዎችን አሳልፏል። ምክር ቤቱ በቀዳሚነት የተወያየው፣ የሀረሪ ብዙኃን መገናኛ ኤጀንሲን የሀረሪ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ በሚል ስያሜ እንደገና ለማቋቋም በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው። ይህም የተቋሙን ሥልጣንና ተግባራት የሕዝብ ብሮድካስት አገልግሎት ተቋማት በአሁኑ ወቅት ከደረሱበት የዕድገት ደረጃ ጋር ማጣጣም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ሲሆን፤ ተቋሙ በብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ ደረጃ ተደራጅቶ በብቃት፣ በጥራትና በውጤታማነት እንዲሠራ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። ካቢኔው በረቂቅ አዋጁ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በማከል፣ እንዲጸድቅ ለክልሉ ምክር ቤት መርቶታል። መስተዳድር ምክር ቤቱ በሁለተኛነት የተወያየበት አጀንዳ፣ የፍልሰት ጉዳዮች አስተባባሪ ምክር ቤትና የትብብር ጥምረትን ለማቋቋም በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ ያተኮረ ነበር። ደንቡ ከክልሉ ነባራዊ ሁኔታ በመነሳትና አግባብነት ያላቸውን አካላት ያቀፈ ክልላዊ የፍልሰት ጉዳዮች አስተባባሪ ምክር ቤትና የትብብር ጥምረትን በማቋቋም፤ በሰው የመነገድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር፣ እንዲሁም የወንጀል ድርጊቱን በሚፈጽሙ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን እንደሚያስችል ተመላክቷል። ከዚህ በተጨማሪም የሕብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያግዝ አደረጃጀት በመፍጠር፣ የዜጎችን ተጋላጭነት የሚቀንሱ ተግባራትን ለማከናወንና ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት እንደሚያግዝ ተገልጿል። የመስተዳድር ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል። ቀጥሎም ምክር ቤቱ የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን ሥርዓትን ለማሻሻል በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ ውይይት አድርጓል። ደንቡ ቀደም ሲል ተግባራዊ በተደረገው ክልላዊ የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ሥርዓት የተጀመሩ አበረታች ሥራዎችን ማሻሻልን ያለመ ሲሆን፤ በተበታተነ መልኩ ሲተገበር የቆየውን አሠራር በተቀናጀ ሁኔታ በሁሉም የክልሉ የአስተዳደር እርከኖች አስተሳስሮ ለመምራት፣ እንዲሁም በክልሉ ሕብረተሰብ መካከል ያለውን የእርስ በእርስ የመደጋገፍ ባሕል በማጠናከር ፍትሐዊ፣ ጥራትና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የታለመ ነው። ከዚህም በላይ በማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ሥርዓት ውስጥ ተሳታፊ የሆኑ አስፈጻሚ አካላትን ተግባርና ኃላፊነት በግልጽ በማስቀመጥ፣ የሀብት አሰባሰብ ሥርዓትንና ተጠያቂነት የሰፈነበት የፋይናንስ አጠቃቀምን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል። መስተዳድር ምክር ቤቱ በዚህ ረቂቅ ደንብ ላይም በሰፊው ከተወያየ በኋላ ሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል። የካቢኔው የማጠቃለያ አጀንዳ የነበረው፣ የቱሪዝም ኮሚሽን ለማቋቋም በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ የመከረበት ጉዳይ ነው። የሀረሪ ክልል በዩኔስኮ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ ሁለት ቅርሶችን ጨምሮ፣ የበርካታ ቁሳዊና መንፈሳዊ ቅርሶች ባለቤት ናት። የቱሪዝም ዘርፍ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያበረክተውን ድርሻ ለማሳደግ፣ በአዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማትና በኢኮ-ቱሪዝም ዘርፍ ውጤቶችን ለማስመዝገብ፣ ዘርፉን በተቀናጀና በባለቤትነት የሚመራ ተቋማዊ አደረጃጀት እንዲኖረው ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል። ለዚህም የቱሪዝም ዘርፉን በራሱ የሚመራ፣ ከበጀትና ከሰው ኃይል አስተዳደር አንጻር ተቋማዊ ነጻነት ያለው የቱሪዝም ኮሚሽን ማቋቋም የዘርፉን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተገልጿል። የመስተዳድር ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል።
የጠቅላላ ምርጫው ስኬት ኢትዮጵያዊያን ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ለዓለም ያስመሰከሩበት ነው
Jun 8, 2026 400
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ስኬት ኢትዮጵያዊያን ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ለዓለም በድጋሜ ያስመሰከሩበት ትልቅ ሀገራዊ ሁነት መሆኑን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ ገለጹ። የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተስተጋቡ አሉታዊ ዘገባና ስሁት ምኞቶችን ያመከነ ታሪካዊ ድል መሆኑን ተናግረዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ ውሎ፤የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎችም እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ ተካሂዶ ፍፃሜውን አግኝቷል። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ ለኢዜአ እንደገለጹት፥የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተስተጋቡ አሉታዊ ዘገባና ስሁት ምኞቶችን ያመከነ ታሪካዊ ድል ነው። በምርጫ ሂደቱም የኢትዮጵያ ህዝብ ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ በመምረጥ መንግሥትን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ መመስረት እንደሚችል በተግባር ማሳየቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ሥርዓትና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ለዓለም ማስመስከሩን ተናግረዋል። በውጭ ዓለማት ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎችም የዜጎች የምርጫ ንቁ ተሳትፎ የዴሞክራሲ ባህል እያበበ መምጣቱን እንዳስገነዘበ አንስተዋል። በተቃራኒው የኢትዮጵያን በጎነት የማይሹ ውስን አካላት ያስተጋቡት ከንቱ ጩኸት በኢትዮጵያዊያን የነቃ ተሳትፎ መምከኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ በውጭ ሀገራትና የዲሞክራሲ ልምምድ በጎለበተባቸው ሀገራት የሚኖሩ ዲያስፖራዎች ጥያቄ ጭምር እንደነበር አንስተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው የኢትዮጵያዊያን ንቁ ተሳትፎም የዲሞክራሲ ሥርዓት ባህል ግንባታና ልምምድን ዳያስፖራው ማህበረሰብ በአዎንታ እንደሚመለከተው ጠቅሰዋል። በምርጫው ተሳትፎ ህዝቡ ለሀገር ግንባታና ሁለንተናዊ ዕድገት ያለውን ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት ለዓለም ህዝብ በተግባር ማሳየቱን አብራርተዋል። በውጭ ዓለማት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የሀገራቸውን ብዝኅ የዕድገት ተስፋ በመመልከትና በመጎብኘት በተፈጠረው የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።
ከየትኛውም ታጣቂ ቡድን ጋር ግንኙነት የለኝም - ኦብነግ
Jun 8, 2026 699
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ) ፦ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ውድቅ አደረገ። ኦብነግ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለገባው የሰላም ስምምነት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነትም አረጋግጧል። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ፤ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ፈጽሞ እንደማይተባበር፣ ስለ ድርጅቱ ወቅታዊ የአመራር ለውጥ እና በትክክለኛ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ መደገፍ ስለሚያስፈልግበት ሁኔታ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል። ኦብነግ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡- የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን በጽኑ የሚቃወም ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለተፈረመው የሰላም ስምምነት ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋግጣል፤ የስምምነቱን ድንጋጌዎች በሙሉ ለማክበር እና ተግባራዊ ለማድረግ ያለውን ዝግጁነትም ያረጋግጣል። በተመሳሳይ ኦብነግ የኢትዮጵያ መንግሥት የገባውን ቃል እንዲያከብር እና የስምምነቱን ሙሉ አፈጻጸም በቅን ልቦና እንዲያረጋግጥ ይጠብቃል። በጥቅምት 21 ቀን 2018 በአስመራ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዛሬ በሶማሊ ክልል ለሚታየው ሰላምና መረጋጋት እንደ መሠረት ሆኖ አገልግሏል። ስምምነቱ ከተተገበረበት ጊዜ ጀምሮ ክልሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሰላማዊና የተረጋጉ ክልሎች አንዱ ለመሆን የበቃ ሲሆን፣ ይህም የስምምነቱን አስፈላጊነት እና ሁሉም ወገኖች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል። ኦብነግ የአስመራው የሰላም ስምምነት ለሶማሊ ክልልና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ጥቅም እንዳስገኘ ያምናል። ከዚህም በላይ ኦብነግ በታሪኩ ሲታገላቸው የነበሩ በርካታ ዓላማዎች እንዲሳኩ አወንታዊ አስተዋጽኦ አድርጓል። በመሆኑም ኦብነግ በሶማሊ ክልል የተገኘውን ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት ሊያናጋ የሚችል ማንኛውንም ድርጊት ወይም ባህሪ በጥብቅ ይቃወማል። እንዲሁም በሰላም ስምምነቱ አማካኝነት የግል ፍላጎታቸውን ማሳካት ያቃታቸው ጥቂት ግለሰቦች አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ በመሞከር የድርጅቱን ስም ያለፈቃድ መጠቀማቸውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ያደርጋል። ኦብነግ መሰል ጥረቶች የድርጅቱን መርሆዎች እንደማያንጸባርቁ ወይም የሶማሊ ክልልን እና የሕዝቡን ጥቅም እንደማያገለግሉ ያምናል። ይልቁንም እነዚህ ጥረቶች በክልሉ የተገኘውንና በብዙ ልፋት የመጣውን ሰላምና መረጋጋት ጥርጥር የሌለው አደጋ ላይ የሚጥሉ ሲሆን፣ ከክልሉ ውጪ የሆኑና ከሶማሊ ክልል ሕዝብ ሕጋዊ ምኞት ጋር የሚጋጩ አጀንዳዎችን የሚያራምዱ ናቸው። በተጨማሪም ኦብነግ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ መንግሥት ለመጣል ዓላማ ካላቸው ሌሎች ድርጅቶች ጋር ምንም ዓይነት ጥምረት እንዳልመሠረተ ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ግልጽ ማድረግ ይሻል። በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት በኃይል ለማስወገድ መታገል ወይም ብቸኛ ዓላማቸው የመንግሥትን ሥልጣን በትጥቅ መያዝ ከሆኑ ድርጅቶች ጋር መሳተፍ የኦብነግ ዓላማ ሆኖ አያውቅም። የኦብነግ ተልዕኮ ሁልጊዜም የሶማሊ ክልል ሕዝቦችን መብት፣ ጥቅም እና ምኞት ማስከበር ላይ ያተኮረ ነው። እነዚህን ዓላማዎች በውይይት እና በጋራ ስምምነት መርሆዎች ላይ በመመሥረት፣ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለማሳካት ቁርጠኛ ሆኖ ይቀጥላል። ስለሆነም ኦብነግ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በግጭት ውስጥ ከሚሳተፉ የታጠቁ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት፣ ትብብር ወይም ተሳትፎ እንደሌለው በድጋሚ ያረጋግጣል። ኦብነግ ለሰላማዊ ግንኙነቶች ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን፣ የሶማሌ ክልልን ሰላም፣ መረጋጋት እና የሕዝብ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም ድርጊቶች ውድቅ ያደርጋል። ኦብነግ አክሎም ከድርጅቱ ምንም ዓይነት ውክልና እና ፈቃድ ሳይኖራቸው በተናጠል በንቀሳቀሱት የቀድሞው የፓርቲው ሊቀመንበር በአቶ አብዲራህማን ማህዲ አማካኝነት የድርጅቱ ስም ያለአግባብ ጥቅም ላይ መዋሉን ያብራራል። አቶ አብዲራህማን ማህዲ በአሁኑ ወቅት በኦብነግ ፓርቲ ውስጥ ምንም ዓይነት የአመራር ቦታ የሌላቸው ሲሆን፣ ፓርቲውን፣ ፖሊሲዎቹን ወይም ዓላማዎቹን አይወክሉም። እ.አ.አ በሰኔ 2025 በጅጅጋ በተካሄደው የኦብነግ ጉባኤ ላይ አቶ አብዲራህማን ማህዲ ከሊቀመንበርነት ኃላፊነታቸው በይፋ የተነሱ ሲሆን፣ አቶ አብዲካሪም ሼክ ሙሴ የኦብነግ ፓርቲ አዲስ ሊቀመንበር ሆነው በሥርዓቱ ተመርጠዋል። በመሆኑም ከዚያ ቀን በኋላ በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የተወሰዱ ማናቸውም እርምጃዎች፣ የተላለፉ ውሳኔዎች ወይም የተሰጡ መግለጫዎች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ አቋም የማይወክሉ በመሆናቸው እንደ ግል አመለካከታቸውና ተግባራቸው ሊቆጠሩ ይገባል። የኦብነግ ፓርቲ @ONLFofficial በሚል የሚታወቀው የኤክስ (የቀድሞው ትዊተር) አካውንት የፓርቲው ይፋዊ አካውንት እንዳልሆነ መግለጽ ይወዳል። ይህ አካውንት በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የሚተዳደር የግል አካውንት ሲሆን፣ በዚህ አካውንት አማካኝነት የሚታተሙ ይዘቶች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ ፖሊሲዎች፣ አቋሞች ወይም መግለጫዎች አይወክሉም። ኦብነግ ሁሉም የሚመለከታቸው ወገኖች፣ ደጋፊዎች፣ የሚዲያ ድርጅቶች እና የሕዝብ አባላት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ስለ ፓርቲው አቋም እንዲሁም እንቅስቃሴዎች መረጃ ለማግኘት በይፋ በተፈቀዱ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ እንዲደገፉ ያሳስባል።
ማህበራዊ
የአፍሪካ እና አውሮፓ የጤና እና ሰብአዊ ፈተናዎች ምላሽ አጋርነት
Jun 8, 2026 116
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ ህብረት ከአፍሪካ ጋር ያለውን የጤና እና ሰብአዊ ፈተናዎችን የመከላከል አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኝነቱን ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የአውሮፓ ህብረት የእኩልነት፣ ዝግጁነት እና የቀውስ አስተዳደር ኮሚሽነር ሃጃ ላህቢብን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። የአውሮፓ ህብረት ለዓለም አቀፍ የጤና ፈተናዎች እያደረገ ያለውን ድጋፍ ያነሱት ሚኒስትሩ፣ በተለይም የኢቦላ ወረርሽኝን ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው የጋራ እንቅስቃሴ ህብረቱ ላሳየው አጋርነት ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል። ህብረቱ የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (Africa CDC) ያደረገው ድጋፍ፣ ሊከሰቱ የሚችሉ ዓለም አቀፍ የጤና ስጋቶችን በጋራ ለመከላከል ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለኮሚሽነሯ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ኮሚሽነር ሃጃ ላህቢብ በበኩላቸው፤ የአውሮፓ ህብረት ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የጋራ መፍትሄ የሚሹ የጤና እና የሰብአዊ ፈተናዎችን በትብብር ለመፍታት ህብረቱ ዝግጁ እንደሆነ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕውቀትን ለትውልድ የሚያሻግር ምኅዳር እየገነባ ነው
Jun 8, 2026 142
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕውቀትን ለትውልድ የሚያሻግር ምኅዳር እየገነባ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገለጹ። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ40 በላይ የመጽሐፍት አከፋፋዮች፣ አሳታሚዎችና የመጽሕፍት መደብሮች የሚሳተፉበትን 18ኛውን ዓመታዊ የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ በስድስት ኪሎ ግቢ ይፋ አድርጓል። ከሰኔ 1 ቀን እስከ ሰኔ 7/2018 ዓ.ም የሚቆየው ዓውደ ርዕይም በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች የሚያተኩሩ ነባርና አዳዲስ መጽሐፍት ለአንባቢያን በቅናሽ ዋጋ ቀርበዋል፤ አዳዲስ መጽሐፍትም ይመረቃሉ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት፤ የዩኒቨርሲቲው ፕሬስ ከ50 ዓመታት በላይ በርካታ መጽሐፍትን ሲያሳትምና ተደራሽ ሲያደርግ ቆይቷል ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ጉዞም የፕሬስ አቅምን በማጎልበና የዘመን ገበያን በመጠቀም የመጽሐፍትን ተደራሽነት የሚያሰፉ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም አርቲፊሻል ኢንተለጀንስና ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕውቀትን ለትውልድ የማሻገርና ተቋሙ ከሌሎች መሰል ተቋማት ጋር ያለውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እንደሚሠራ ገልጸዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ደርብ አዶ (ዶ/ር)፤ ዓውደ ርዕዩ የመጽሐፍት ሽያጭ፣ የደራሲያን የልምድ ልውውጥ፣ ውይይትና የፕሬስ ሕትመቶች ምርቃት ይካሄድበታል ብለዋል። በቀጣይም የዩኒቨርሲቲውን ፕሬስ ዓለም አቀፍ ተደራሽነት የሚያሰፉ ተግባራትን የበለጠ ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። በዓውደ ርዕዩ ከተሳተፉት መካከል የክብሩ መጽሐፍት መደብር ተወካይ ሜሮን ይልማ፤ ዓውደ ርዕዩ የንባብ ባህል እንዲሁም የተጠቃሚዎችን ቁጥር ለማሳደግ መነቃቃት የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ሕፃናት በጨዋታ መልክ የሚያስተምሩ መጫወቻዎችን ይዘው የቀረቡት የፊት በር ቶይስ ተወካይ ሚካኤል ግርማ በበኩላቸው፤ ዓውደ ርዕዩ ምርታቸውን ለማስተዋወቅ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ መምህር ሶንግ ሩዶንግና ዩሊያን ዡ ዩሉ በበኩላቸው፤ ዓውደ ርዕዩ ተማሪዎች መጽሐፍት እንዲያገኙና የንባብ ባህል እንዲያዳብሩ የሚያስችል ነው ብለዋል። ዓውደ ርዕዩው በርከት ያሉ መጽሐፍት የቀረቡበት በመሆኑ አንባቢያን የሚፈልጉትን እንዲያገኙ ያስችላል ያሉት ደግሞ መህዲ አብዱረዛቅና ጅሎ ከሚ ናቸው። በዓውደ ርዕዩ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አምባሳደር ቶፊቅ አብዱላሂ (ዶ/ር)፤ ዓውደ ርዕዩ የንባብ ባህልን በማዳበር ወጣቶችና ታዳጊዎች ዕውቀት ማሳደግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። በቀጣይም ዜጎች የንባብ ባህላቸውን በማጎልበት በዕውቀትና ምክንያታዊነት የተመሰረተ ዕሳቤን ማበልፀግ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።
በአፋር ክልል የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎትን በማጠናከር ፍትሃዊ አገልግሎት ተደራሽ ይደረጋል
Jun 8, 2026 207
ሰመራ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎትን በማጠናከር ፍትሃዊ አገልግሎት ተደራሽ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ገለፀ። አገልግሎቱ ከአፋር ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በክልሉ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎትን ለማጠናከር በወረዳዎች የተበታተነውን የፋይናንስ አቅም ወደ ክልል ለማምጣት ያለመ የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል። በመድረኩ የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልገሎት ዋና ዳይሬክተር ተስፋዬ ወርቁ ባለፉት ዓመታት ማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ የህብረተሰብ ቁጥር የማሳደግ ስራ ተሰርቷል። በመረዳዳት ላይ የተመሰረተው ማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎትን ለማሳካትም የገንዘብ አቅምን ማሳደግ ላይ ትኩረት መሰጠቱን ገልፀዋል። ለዚህም በክልሉ በ40 ወረዳዎች የሚገኘውን ገንዘብ ወደ አንድ ቋት ለማምጣት መሰራቱ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። ማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎትን ለማሳካት የሚስተዋሉ እጥረቶችን በማረም እንደ ሀገር በያዝነው ዓመት ለ70 ሚሊየን ሰዎች ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የጤናውን ዘርፍ በአግባቡ በመምራት የአገልግሎቱን ተደራሽነትና ጥራት ለማስጠበቅ የሃብት አስተዳደር ወሳኝ ነው ያሉት ደግሞ የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ ያሲን ሃቢብ ናቸው። በክልሉ አንድ የሂሳብ ቋት በማዘጋጀት ጠንካራ የጤና መድህን ስርዓት እየተገነባ መምጣቱን ገልጸው ስራውንም በተደራጀ መንገድ ለመምራት ስልጠናዎች በየጊዜው መሰጠታቸውን አስረድተዋል። ይህም የክልሉን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚነት ቁጥር ማሳደግ መስቻሉን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት የአፋር ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ኢድሪስ መሐመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው አገልግሎቱ በ2012ዓ.ም በክልሉ በአይሳኢታና አፋምቦ ወረዳዎች መጀመሩን አስታውሰው በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱ በ40 ወረዳዎች ተደራሽ መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም 158ሺህ አባወራዎችና እማወራዎችን ተጠቃሚ በማድረግ በክልሉ 80 በመቶውን መሸፈን መቻሉን አስረድተዋል። የህብረተሰቡን ጥያቄ በተሟላ ደረጃ ለመመለስና የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የክልላዊ ቋት ወደ ትግበራ ለማስገባት ለባለድርሻዎች እየተሰጠ ያለው ስልጠና ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በስልጠናው የክልሉ ገንዘብ ቢሮ፣ ሲቪል ሰርቪሰና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ እንዲሁም ከክልሉ ጤና ቢሮ የተውጣጡ ባለሙያዎች እየተሳተፉበት ሲሆን ለሁለት ቀናት የሚቆይ መሆኑም ተገልጿል።
18ኛው ዓመታዊ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጻሕፍት ዓውደ ርዕይ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ በይፋ ተከፈተ
Jun 8, 2026 284
አዲስ አበባ፤ሰኔ 1/2018(ኢዜአ)፦18ኛው ዓመታዊ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጻሕፍት ዓውደ ርዕይ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ በይፋ ተከፍቷል። ዓውደ ርዕዩ ከዛሬ ሰኔ 1 ቀን እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን ከ40 በላይ የመጻሕፍት አከፋፋዮች፣አሳታሚዎችና የመጻሕፍት መደብሮች ተሳትፈውበታል። በዚህ የመጻሕፍት ዓውደ ርዕይ በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ላይ የሚያተኩሩ በርካታ ነባርና አዳዲስ መጻሕፍት ለአንባቢያን በቅናሽ ዋጋ የቀረቡ ሲሆን አዳዲስ መጻሕፍትም ይመረቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ላለፉት ከ50 ዓመታት በላይ በርካታ መጻሕፍትን ሲያሳትምና ተደራሽ ሲያደርግ ቆይቷል። ዩኒቨርሲቲው ወደ ራስ ገዝነት በሚያደርገው ጉዞም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስን አቅም የማሳደግና የዘመኑን ገበያ በመጠቀም ተደራሽነቱን የሚያሰፉ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። በቀጣይም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስና ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕውቀትን ለትውልድ የማሻገርና ተቋሙ ከሌሎች መሰል ተቋማት ጋር ያለውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እንደሚሠራ ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
በጅማ ዞን የተጀመረው የሻይ ቅጠል ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው
Jun 8, 2026 263
ጅማ፣ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የተጀመረው የሻይ ቅጠል ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያሳድግ መሆኑን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ተናገሩ። በዞኑ ሸቤ ሶምቦ ወረዳ አርሶ አደሩን ባሳተፈ መልኩ የሻይ ቅጠል ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር እንደገለጹት፤ ዞኑ ለሻይ ቅጠል ልማት ምቹ በመሆኑ አርሶ አደሩን በክላስተር በማደራጀትና አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሠራ ይገኛል። በዞኑ ከ 60 ሚሊዮን በላይ የሻይ ቅጠል ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ 20 ሚሊዮን የሚበልጠውን የመትከል ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በ 1 ሺህ 600 ሄክታር መሬት ላይ የሻይ ቅጠል ማልማት መቻሉን ጠቅሰው፤ የሻይ ቅጠል ልማቱን ይበልጥ አስፋፍቶ ምርቱን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል የሻይ ቅጠል ፋብሪካ የማቋቋም ሥራ በትኩረት እየተሠራበት ይገኛልም ነው ያሉት። የሸቤ ሶምቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ መሐመድሳኒ አባ ኦሊ በበኩላቸው፤ በወረዳው በአሁኑ ወቅት በ 500 ሄክታር መሬት ላይ የሻይ ቅጠል እየለማ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም በኩታ ገጠም ተደራጅተው ወደ ሥራው ለገቡ አርሶ አደሮችና ወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል መፈጠሩንና ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን አክለዋል። የወረዳው አርሶ አደሮች የሆኑት አባ ዝናብ አባዋይ እና አህመድ ሼከማል በኩታ ገጠም ተደራጅተው በሻይ ቅጠል ልማት ላይ መሰማራታቸውን ገልጸው፤ ከባለሙያዎች የሚደረግላቸው ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑንና ወደ ሥራው በመግባታቸው ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ተናግረዋል። ሌላኛው ወጣት አርሶ አደር ሚፍታህ መሐመድ በበኩሉ፤ በአሁኑ ወቅት ከሌሎች ወጣቶች ጋር ተደራጅቶ የሻይ ቅጠል እያለማ መሆኑን ጠቅሶ ወደ ፊት ተጠቃሚ እንደምሆን ትልቅ ተስፋ አለኝ ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።
የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ በወተት ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ነው
Jun 8, 2026 178
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ)፦ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ በወተት ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ደኤታ ኢፋ ሙለታ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በባዮ ቴክኖሎጂ ምርምር "ኢቲቱ" የተሰኘ ወተት ማርጋት የሚያስችል የፕሮ ባዮቲክ እርሾ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዓለም የወተት ቀንን አስመልክቶ የጋራ የውይይት መድረክ እና አውደ-ርዕይ አካሂዷል። የግብርና ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ደኤታ ኢፋ ሙለታ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ "ኢቲቱ" የፕሮ ባዮቲክ እርሾ ከውጭ የሚገባውን ምርት በማስቀረት የውጭ ምንዛሪን ማዳን የሚያስችል ነው፡፡ ይህም በወተት እና የወተት ተዋጽኦ ምርታማነት ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ በግብርና ፖሊሲ የምግብ ዋስትናንና ስነ-ምግብን ለማጠናከር እያከናወነች ያለውን ስራ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተተገበረው የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ በወተት ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ባለሀብቶች በዘርፉ እንዲሰማሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረው በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረገው "ኢቲቱ" የፕሮ ባዮቲክ እርሾ አምራቹን እና የዘርፉን ተዋንያን የሚያነቃቃ መሆኑን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ንጉሴ ደቻሳ በበኩላቸው "ኢቲቱ" የተሰኘው አዲሱ የፕሮ ባዮቲክ እርሾ በሀገሪቱ ያሉ የወተት ማቀነባበሪያ ድርጅቶች በውጭ ምንዛሪ ከውጭ አስገብተው የሚጠቀሙበትን እርሾ የሚተካ ነው ብለዋል። ይህ የምርምር ውጤት የውጪ ምንዛሪ ወጪን ከማዳን ባለፈ፣ ፓስቸራይዝድ የሆነ ወተትን በአራት ሰዓታት ውስጥ ማርጋት ያስችላል ነው ያሉት። ኢንስቲትዩቱ ምርምር ከሚያደርግባቸው የግብርና ውጤቶች መካከል ወተትና የወተት ተዋጽኦዎች ዋነኞቹ መሆናቸውን ገልጸው፤ ምርቱ ለምግብ ዋስትና እና ለጤንነት ወሳኝ የሆኑ ንጥረ ነገሮችን የያዘ መሆኑን አብራርተዋል። ኢንስቲትዩቱ የተሻሻሉ የሰብል እና የእንስሳት ዝርያዎችን በምርምር በማውጣት ለዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም በወተት ምርታማነት ላይ ትኩረት ያደረጉ በባዮ ቴክኖሎጂ የታገዙ ልዩ ልዩ ምርምሮች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። "ኢቲቱ" የፕሮ ባዮቲክ እርሾ ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያረጋግጥ የገለጹት ደግሞ የሰበታ አግሮ ኢንዱስትሪ ዋና ስራ አስፈጻሚ እና የኢትዮጵያ ዴይሪ ማህበር ፕሬዝደንት ሙልጌታ ይመር ናቸው። እንዲሁም የምርት ሂደትን የሚያፋጥንና በሀገር ውስጥ መመረቱ ተደራሽነቱንም የሚያረጋግጥ መሆኑን አንስተዋል። የዓለም የወተት ቀን የወተት ምርት ለሥነ-ምግብ እንዲሁም ለኢኮኖሚ ያለው ፋይዳ የሚታሰብበት ሲሆን፣ ዕለቱ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ እና የግብርና ድርጅት (FAO) አማካኝነት እ.ኤ.አ በ2001 የተቋቋመ ዓለም አቀፍ ሁነት መሆኑ ይታወቃል።
የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የኑሮ ጫናን በመቀነስና ገበያን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ እፎይታ እየሰጡ ነው
Jun 8, 2026 148
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የኑሮ ጫናን በመቀነስና ገበያን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ እፎይታ እየሰጡ መሆኑን አስተያየታቸውን የሰጡ ሸማቾችና ነጋዴዎች ገለጹ። መንግሥት በቅዳሜና እሁድ ገበያዎችና ተግባራዊ ባደረጋቸው የተለያዩ ኢኒሼቲቮች የምርት አቅርቦትን በማሳደግ፣ የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር፣ ገበያን በማረጋጋት እንዲሁም የኑሮ ጫናን በማቃለል የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል። የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ዋነኛ ዓላማም ሸማቾች ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ማስቻል ሲሆን፤ ገበያዎቹ ምርቶቹን ከአርሶ አደሮች፣ ከፋብሪካዎች ወይም ከሸማቾች የኅብረት ሥራ ማህበራት በቀጥታ በመረከብ እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ኢዜአ በመዲናዋ በሚገኙ የተለያዩ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው ሸማቾችና ነጋዴዎች በገበያዎቹ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያገኙና እያቀረቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡት ሸማቾች መካከል አቶ አውላቸው ይልማ እንደገለጹት፤ የሚፈልጉትን ምርት በበቂና በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት ችለዋል። የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በአካባቢያቸው መከፈታቸው ለግብይት የሚያስፈልገውን ጊዜና የትራንስፖርት ወጪ እንደቆጠበላቸው ገልጸው፤ የገበያዎቹ በቅርብ ርቀት ተደራሽ መሆን ተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ የፈለጉትን ምርት እንዲያገኙ ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ሞልቶታል ጫንያለው በበኩላቸው፤ በመዲናችን አዲስ አበባ በየሳምንቱ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎችን የሚያስተናግዱና ለከተማዋ ትልቅ እፎይታን የሚሰጡ የገበያ ስፍራዎች ሆነዋል ብለዋል፡፡ የቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላት የከተማዋን ነዋሪ የኑሮ ጫና ለማቅለል እና ገበያ ለማረጋጋት ትልቅ አቅም መሆናቸውንም ጠቅሰው ምርቶችን በቀጥታ ለህዝቡ እንዲቀርቡ በማድረግ የዋጋ ንረትን በማረጋጋት ረገድም ገበያዎቹ ጉልህ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። መንግስት ሸማቹንና አምራቹን በቀጥታ ለማገናኘትና የኑሮ ውድነቱን ጫና ለማቃለል የወሰደው ይህ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ማቋቋም እርምጃ፤ በማህበረሰቡ ዘንድ ትልቅ እፎይታንና በጎ ምላሽን ያስገኘ መሆኑን ነጋዴዎችም ጭምር ጠቅሰዋል፡፡ በእሁድ ገበያ ላይ በመሳተፍ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን የሚያቀርቡት እነኚሁ ነጋዴዎች፤ ከኅብረት ሥራ ማህበራት እና ከአቅራቢዎች በቂ ምርት እያመጡ ለኅብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጡ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ከነጋዴዎቹ መካከል ዮርዳኖስ መልካሙ እንደገለጹት፤ ገበያው ምርታቸውን በቀጥታ ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማድረስ በእጅጉ እየረዳቸው ይገኛል። ለሸማቹ ማህበረሰብ ከመደበኛው ገበያ ባነሰ ዋጋ ምርቶችን በማቅረብ ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው፣ መንግሥት የገበያ ቦታዎችን በማመቻቸት ምርቶችን ከአቅራቢዎች በቀላሉ በማግኘት ለኅብረተሰቡ ለማቅረብ ማስቻሉን አብራርተዋል። ሌላኛው ነጋዴ መለሰ ካሳው በበኩሉ፤ ይህም ምርቶችን በበቂ እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ ለማቅረብ እጅግ ጥሩ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው አስገንዝቧል። ኅብረተሰቡ በእነዚህ መገበያያ ቦታዎች በመገኘት የሚፈልገውን ምርት በደስታና በእፎይታ እየገዛ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ነጋዴው አወቀ ቦልዲስ ናቸው፡፡ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን በአካባቢያቸው በማገኘታቸው መደሰታቸውን የጠቀሱት አስተያየት ሰጪዎቹ፤ የኅብረተሰቡን ፍላጎት ይበልጥ ለማሟላት የምርት አቅርቦቱን በስፋትና በጥራት ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በ240 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ፍራፍሬ እየለማ ነው
Jun 8, 2026 254
አዲስ አበባ፤ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በ240 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ፍራፍሬ እየለማ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ክልሉ ለፍራፍሬ ልማት ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በበጀት ዓመቱ 29 ሚሊዮን ኩንታል የፍራፍሬ ምርት መመረቱም ተገልጿል። በኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ የፍራፍሬ ልማት ዳይሬክተር አቶ ቻላቸው አዱኛ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በክልሉ ከለውጡ ዓመታት ወዲህ ለፍራፍሬ ልማት ዘርፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ክልሉ ለፍራፍሬ ልማት ምቹ የአየር ንብረት፣ በቂ የዝናብ መጠንና ተስማሚ የአፈር ዓይነት ያለው በመሆኑ ለዘርፉ ምርታማነት ከፍተኛ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል። በተለይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የምግብ ስርዓትን ከማሻሻል ረገድ ሚናው የላቀ በመሆኑ በተሰሩት በርካታ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፣ በዚህም የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እያደገ ነው ብለዋል። ይህንን ተከትሎ እንደ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ማንጎ፣ ብርቱካን፣ አፕል እና ሎሚ ያሉ ዋና ዋና የፍራፍሬ ዓይነቶች የዞኖቹን መልክዓ ምድርና የአየር ንብረት መሰረት በማድረግ በትኩረት እየለማ ነው ብለዋል። ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ምርጥ ዘሮችን በመጠቀምና የማስፈጸም አቅምን በማሻሻል ልማቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በዚህም በ2013 ዓ.ም ከ90 ሺህ ሄክታር ያልበለጠ የነበረው የፍራፍሬ ልማት፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 240 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እየለማ መሆኑን ተናግረዋል። ክልሉ ለፍራፍሬ ልማት ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በበጀት ዓመቱ 29 ሚሊዮን ኩንታል የፍራፍሬ ምርት መመረቱንም ተናግርዋል። ከዚህ ውስጥም ከ8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የሚሆነው የአቮካዶ ምርት መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት 2 ሺህ 400 ኩንታል የአቮካዶ ምርት ወደ ውጭ መላኩን አንስተው፣ ዘንድሮም በተሻለ ሁኔታ ለመላክ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። አርሶ አደሮቹ የግብርና ኤክስቴንሽን ፓኬጁን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲያደርጉ የተለያዩ ሙያዊ ድጋፎችና ስልጠናዎች እየተሰጧቸው መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 8, 2026 273
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፤ ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው ብለዋል። 9ኛው አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ ዛሬ መጀመሩንም አስታውቀዋል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ለህዝቡ ቃል በተገባው መሰረትም የዛሬውን ጨምሮ ዘጠኝ ማዕከላትን ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ጠቁመዋል። ይህ አሰራር የአገልግሎት እንግልትን፣ ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅረፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝብን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ነው ያብራሩት። ህዝቡ ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል ለማድረግ የታቀደውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ከንቲባዋ ገልጸዋል። በየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ላደረጉት አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Jun 8, 2026 222
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ። ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ በየካ ክፍለ ከተማ የተገነባውን 9ኛ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል። ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ በዚሁ ወቅት፤ የማዕከሉ መገንባት ህብረተሰቡ ፈጣን፣ ግልጽ እና ፍትሐዊ አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል ነው ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ ቀደም ሲል ከህዝብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች የአገልግሎት አሰጣጥ ውስንነት የህዝብ እንግልትና ምሬት ምንጭ መሆናቸውን ማረጋገጥ መቻሉን አውስተዋል። ለህዝብ ጥያቄ ቅድሚያ መስጠት ዋና መገለጫ የሆነው ከተማ አስተዳደሩ፤ ጥራት ላለው የመንግሥት አገልግሎት እንቅፋት የሆኑ ምክንያቶችን ነቀሶ በማውጣት እልባት እየሰጠ መምጣቱን ተናግረዋል። በዚህም አልፎ አልፎ ይስተዋሉ የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት አንዱና ዋነኛው መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ የዛሬውን ጨምሮ ዘጠኝ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በማደራጀት ወደ ስራ መግባቱን ጠቅሰዋል። እነዚህ ማዕከላት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙላቸው እና የበቃ የሰው ሀይል የተሟሉላቸው መሆናቸውን ገልጸዋል። የማዕከላቱ ወደ ስራ መግባት ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበትን አሰራርን እውን በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ይነሱ የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን መቅረፍ ማስቻላቸውን ነው የተናገሩት። በቀጣይም በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት ዜጎችን ከእንግልትና ከአላስፈላጊ የገንዘብ ወጭ ታድጓል ብለዋል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ ነው
Jun 8, 2026 178
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ)፦ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ገለጹ፡፡ ዶክተር ደረጄ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ የልማት አቅጣጫ በጤናው ዘርፍ ፈጣንና ቀልጣፋ የአገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂም የጤና ተቋማትን አገልግሎት በማዘመን ወሳኝ መሰረት መጣሉን አስታውሰዋል። ለአብነትም የጤና ተቋማትን አገልግሎቶች በኦላይን የዲጂታል ሥርዓት በማሰናሰል ተገልጋዮች ቀልጣፋና ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር የኢንተርኔት አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው አካባቢ የሚገኙ ጤና ተቋማት ጭምር ''በሄልዝ ኔት'' ለማስተሳሰር መሰረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የዲጂታል ጤና አገልግሎቱም የበሽታ መከላከልና አክሞ ማዳን አቅሞችን በማጎልበት ረገድ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ጤና አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማስፋት በተከናወኑ ተግባራትም 40 ሶፍትዌሮችን በማልማት ተገልጋዮች የጤና መረጃና አገልግሎት እንዲያገኙና መረጃን በስፋት እንዲሰንዱ እየተደረገ መሆኑን አንሰተዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል። በቀጣይም በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓት የጤና ምኅዳሩን በዲጂታላይዜሽን የአሰራር ሥርዓት በማሳለጥ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከናወኑ ምርምሮችን ችግር ፈቺ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - የትምህርት ሚኒስቴር
Jun 8, 2026 268
ሮቤ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከናወኑ የምርምር ሥራዎች ችግር ፈቺ፣ ውጤታማና ወጥ አሠራር እንዲኖራቸው በማድረግ፣ ለሀገራዊ የልማት ዕቅድ መሳካት የድርሻቸውን እንዲወጡ የተጀመሩ ሥራዎች እንደሚጠናከሩ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለተመራማሪዎችና ለመምህራን በዘመናዊ የምርምር ማሻሻያ ስትራቴጂዎችና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል። በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ሥራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሐንድሶ (ዶ/ር) በሥልጠናው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲዎች ከመማር ማስተማር በተጓዳኝ ችግር ፈቺ የምርምር ሥራዎችን እያካሄዱ ይገኛሉ። "የሀገራት ዕድገት ዋና ምስጢር ጥራት ያለው የምርምርና የፈጠራ ሥራዎች ውጤት ነው" ያሉት ሥራ አስፈጻሚው፤ ዩኒቨርሲቲዎች ከአካባቢያቸው ባለፈ ለሀገሪቱ የልማት ግብ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማበርከት አለባቸው ብለዋል። ሥልጠናውም ምሁራን በየጊዜው ከሚለዋወጡ ዓለም አቀፋዊ የምርምር ስልቶች ጋር እንዲራመዱ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ተቋሙ ጥራት ያለው ሥልጠና ከመስጠት ጎን ለጎን የተጀመረውን ሀገራዊ ልማት ለመደገፍ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው በበጀት ዓመቱ በትኩረት እየሠራባቸው ከሚገኙ ዋና ዋና የምርምር ዘርፎች መካከል ግብርና፣ ዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ፣ ጤና እና ቱሪዝም ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም፣ ቀደም ሲል በተናጠል ይሰሩ የነበሩ የምርምር ሥራዎችን በማቀናጀት፣ የተሻለ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ ግዙፍ የምርምርና የፕሮጀክት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንና ሥልጠናውም ትልቅ አቅም እንደሚሆን አመልክተዋል። የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክና ምርምር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ (ዶ/ር)፤ ይህ ዓይነቱ ሥልጠና በጀትን በቁጠባ በመጠቀም ተወዳዳሪና ተፅዕኖ ፈጣሪ የምርምር ውጤቶችን ለማፍራት የሰው ኃይል አቅምን እንደሚገነባ ገልጸዋል። ሥልጠናው በተለይም በመሠረታዊ የምርምር ሥርዓትና በምርምር ሥነ-ምግባር፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት አጠቃቀም፣ በምርምር ፈንድ አፈላለግ ስልቶች ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል።
ስፖርት
በሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ ተደረገ
Jun 8, 2026 187
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ራውዳ ዓሊ፣ ቡድኑ በዓለም ዋንጫ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ ከዛምቢያ አቻው ጋር ለሚያደርገው ወሳኝ ጨዋታ ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርበዋል። ከተመረጡት ተጫዋቾች መካከል ግብ ጠባቂዎቹ መቲ ረታ (ልደታ ክፍለ ከተማ) ፣ ኑዳ ሁሴን (አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ) እና ባንቺጊዜ አንተነህ (ኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ) ጥሪ ደርሷቸዋል። ማንጠግቦሽ አድማሱ (አርባምንጭ ከተማ )፣ እየሩሳሌም ኤርሚያስ (መቀሌ 70 እንደርታ)፣ ኤልሻዳይ ዮሴፍ ( ጉለሌ ክፍለ ከተማ) ፣ ቤተልሄም ጌታቸው (ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ)፣ መድኃኒት አለሙ (አርባምንጭ ከተማ)፣ መክሊት መሰለ (ጉለሌ ክፍለ ከተማ) እና ዝናሽ ሰለሞን (ድሬዳዋ ከተማ) በተከላካይ መስመር የሚገኙ ተጫዋቾች ናቸው። በአማካይ ክፍል ናጆክ ዱክ ( የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ)፣ ሊያም ዳንኤል (የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ)፣ ጌጤነሽ ተስፋዬ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ)፣ ቢታኒያ አስተረፍ (ሲዳማ ቡና) ፣ ናግዋ ማን (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ)፣ ኮከብ ደጀኔ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ)፣ ኤልሳ መኮንን (ድሬዳዋ ከተማ) እና ሊዲያ ሰለሞን (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ) በጥሪው ተካትተዋል። ምህረት ወሰኑ (ሸገር ከተማ)፣ ምህረት አየለ (ቦሌ ክፍለ ከተማ) ፣ ሊዲያ ኢያሱ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ) ፣ ሳውያ መሐመድ (ፋሲል ከነማ)፣ እመቤት ዘካሪያስ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ)፣ ኦጁሉ ኦዶንግ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ) እና ሲርያ ተሾመ (ጉለሌ ክፍለ ከተማ) በአጥቂ መስመር ጥሪ ቀርቦላቸዋል። ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም በካፍ የልህቀት ማዕከል በመሰባሰብ ዝግጅት ማድረግ እንደሚጀምሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዛምቢያ ጋር የመጨረሻ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ሰኔ 27 እና ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ያደርጋል። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ 24 ሀገራት ይሳተፋሉ። በዓለም ዋንጫው አፍሪካ ሞሮኮን ጨምሮ በአምስት ሀገራት ትወከላለች። ከሞሮኮ ውጪ በማጣሪያ የሚያልፉ አራት የአፍሪካ ሀገራት በመጨረሻ ዙር ጨዋታዎች ይለያሉ።
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ከዛምቢያ ጋር ጨዋታ የሚያደርግባቸው ቀናት ታውቀዋል
Jun 8, 2026 233
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/ 2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ዓለም ዋንጫ ማጣርያ የመጨረሻ ዙር ማጣርያ ጨዋታዋን ከዛምቢያ ጋር ሰኔ 27 እና ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ታደርጋለች። በዚሁ መሰረት የመጀመሪያው ጨዋታ ዛምቢያ ላይ፣ የመልሱ ጨዋታ በኢትዮጵያ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በሁለተኛው ዙር ማጣሪያ ኢትዮጵያ ብሩንዲን፣ ዛምቢያ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን በደርሶ መልስ ውጤት አሸንፈዋል። ኢትዮጵያ በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈች በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ዓለም ዋንጫ ትሳተፋለች። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ 24 ሀገራት ይሳተፋሉ። በዓለም ዋንጫው አፍሪካ ሞሮኮን ጨምሮ በአምስት ሀገራት ትወከላለች። ቀሪ አራት ሀገራት በማጣሪያ ጨዋታዎች ይለያሉ።
በዓለም አቀፍ ውድድሮች የቀጠለው የኢትዮጵያ አትሌቶች ድል
Jun 7, 2026 822
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዓለም አቀፍ ውድድሮች ድል ማስመዝገባቸውን ቀጥለዋል። በብራዚል በተካሄደው የሪዮ ዴ ጃኔይሮ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታዎች ድል ሲቀዳጁ፣ በስቶኮልም ዳይመንድ ሊግ ደግሞ አትሌት ብርቄ ሓየሎም አሸናፊ ሆናለች። ዛሬ በተካሄደው የዘንድሮው የሪዮ ዴ ጃኔይሮ ማራቶን ውድድር፣ በሴቶች አትሌት ጋዲሴ ሙሉ 2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ46 ሴኮንድ አሸናፊ ሆናለች። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 5ኛ ያለውን ደረጃ በአጠቃላይ በመቆጣጠር ፍጹም የበላይነታቸውን አሳይተዋል። አትሌት ትርፌ ፀጋዬ 2ኛ፣ አትሌት አዝመራ አብረሃ 3ኛ፣ አትሌት አፍራ ጉዳፈይ 4ኛ እና ዝናሽ ደበበ 5ኛ ደረጃን ይዘው ጨርሰዋል። በወንዶች አትሌት ፀጋዬ ጌታቸው በአስደናቂ አጨራረስ ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቋል። ፀጋዬ ውድድሩን ለመጨረስ 2 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ የወሰደበት ሲሆን፣ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት አንተንአየሁ ይስማ በሴኮንድ ልዩነት ተበልጦ ሁለተኛ መሆን ችሏል። በሌላ በኩል በስዊድን ስቶኮልም በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት ብርቄ ሓየሎም በ1500 ሜትር አሸንፋለች። ብርቄ ከሁለት ቀናት በፊት በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደው ተመሳሳይ የርቀት ውድድር በአንደኝነት ማጠናቀቋ የሚታወስ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ በአጭር የሰዓታት ልዩነት 4:00.68 በስቶኮልም ዳግም በማሸነፍ አስደናቂ ብቃቷን አሳይታለች። በዚሁ ውድድር ላይ የተካፈለችው ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሐረገወይኒ ካላዩ ውድድሩን አራተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል።
በ19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ጌታቸው ማስረሻና አትሌት መሰለች አለማየሁ አሸነፉ
Jun 7, 2026 629
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፦ 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ዛሬ ረፋድ ላይ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ ተካሂዷል። በወንዶች ውድድር የሸገር ሲቲው አትሌት ጌታቸው ማስረሻ አንደኛ በመውጣት በድል አጠናቋል። ባየልኝ ተሻገር ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ሁለተኛ፣ በላይ ጥላሁን ከአዲስ አበባ አትሌቲክስ ክለብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸናፊ ሆናለች። ዝማም ባራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ የሸገር ሲቲዋ በቀለች ተኩ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። በ19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳታፊ ሆነዋል። የውድድሩ ዋና አላማ በዴንማርክ ኮፐንሃገን በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም ለሚካሄደው 26ኛው የዓለም አትሌቲክስ የግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች መምረጥ እና ተተኪዎችን ማፍራት ነው። በውድድሩ ላይ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ አትሌቶች የገንዘብ፣ሜዳሊያና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የዘንድሮው ውድድር ተሳታፊዎች ብዛት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የ434 አትሌቶች ጭማሪ ማሳየቱን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
አካባቢ ጥበቃ
በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል
Jun 8, 2026 223
ባህር ዳር፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን የክልሉ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። ዓለም አካባቢ ቀን "የአየር ንብረት ለውጥ ተጽኖን መታደግ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የባለስልጣኑ ዋና ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ በመድረኩ እንደገለጹት፣ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያገዘ ነው። የኮሪደር ልማትም ከተሞችን ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ በማድረግ የአካባቢ ጥበቃንና እንክብካቤ ሥራ እንዲፋጠን አስተዋጾ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ማንኛውም የልማት ፕሮጀክት ዘላቂነቱ የሚረጋገጠው ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በተጣጣመ መልኩ ሲተገበር መሆኑን ገልጸው፣ ይህም በክልሉ ተግባራዊ መደረጉን ጠቁመዋል። በክልሉ የልማት ሥራዎች ከአየር ንብረት ጋር ተጣጥመው እንዲከናወኑ መደረጉ እንደ ጎርፍ እና በረሀማነት ያሉ ችግሮችን ለመቀነስ መቻሉን ተናግረዋል። በአማራጭ የሃይል አቅርቦት ላይ የተመሰረተ ልማትም የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን አስረድተዋል። የአካባቢ ብክለትን ለመከላከልም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለህብረተሰቡ በዘመናዊ ቆሻሻ አወጋገድ ላይ ትምህርት በመስጠት ለውጥ እየታየ መምጣቱን ጠቁመዋል። ይህም ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በባለስልጣኑ የአየር ንብረት ለውጥ አካቶ ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አወቀ ይታይ የመወያያ ጽሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በግብርና፣ በትራንስፖርትና በከተማ ልማት ዘርፎች የአየር ንብረት ጉዳይን አካቶ እየተሰራ ነው። በማሳያነትም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና በኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።
በክልሉ በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለመኸር እርሻ አመች ነው
Jun 8, 2026 238
ጋምቤላ፤ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለመኸር እርሻው አመች መሆኑን በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋምቤላ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ለ2018 ዓ.ም የክረምት ወቅት ያወጣው ትንበያ እንደሚያሳየው፣ በዘንድሮው መኸር የሚኖረው የዝናብ ስርጭት መደበኛና ለአዝመራው አመቺ እንደሚሆን ይጠበቃል። ይህ መረጃ ክልሉ ካለው ሰፊ የሩዝ፣ የበቆሎና የጥራጥሬ ሰብሎች ልማት አቅም አንጻር አርሶ አደሩና የኢንቨስትመንት አካላት አስቀድመው እንዲዘጋጁ ትልቅ እገዛ ያደርጋል። የጋምቤላ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋሁን ዓለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው ዝናብ መደበኛና ብዙ ከመደበኛ ያላለፉ የዝናብ ስርጭት እንደሚሆን ይጠበቃል። በክልሉ የሚኖረው የዝናብ ስርጭት በአብዛኛው መደበኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለመኸር እርሻው መሳለጥ ዓይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በተለይም አርሶና ከፊል አርብቶ አደሩ የግብርና ልማቱን ለማከወንና ለመከታተል ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር መሪ ስራ አስፈፃሚው ገልጸዋል። በአንፃሩ የዝናቡ ዝርጭት በአብዛኛው መደበኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለወባ ትንኝ መራባት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ የወባ በሽታ ሊጨምር ስለሚችል አስፈላጊው ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ብለዋል። እንዲሁም አልፎ-አልፎ በሚኖረው ከመደበኛ ያለፈ የዝናብ ስርጭት ቅጽበታዊ ጉርፍ ሊከሰት ስለሚችልም ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አቶ ተስፋሁን አስገንዝበዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው ተግባራዊ የተደረጉ ፕሮጀክቶች ለአካባቢ ጥበቃ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
Jun 6, 2026 1147
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ የወንዝ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማቶችን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው የተተገበሩ ፕሮጀክቶች ለአካባቢ ጥበቃ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ገለጸ። የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ53ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ ተከብሯል። ቀኑን ምክንያት በማድረግም ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ከተማ የተውጣጡ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የስራ ሀላፊዎች እና ባለሙያዎች ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ የተሰራውን የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቱ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ ክፍት መደረጉ ይታወሳል። የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው የተተገበሩ ፕሮጀክቶች የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው። በአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰው፤ ይህም የአየር ብክለት መቀነስን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች እያስገኘ ነው ብለዋል። ይህም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲቸራት ያስቻለ መሆኑን በመጠቆም፤ ሥነ ምህዳርን በማሻሻል በኩል ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም አብራርተዋል። የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ፕሮጀክት አካባቢ ጥበቃን ውጤታማ እያደረጉ ካሉ ሥራዎች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመው፤ የእንጦጦ ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ለዚህ አይነተኛ ማሳያ ነው ብለዋል። በፕሮጀክቱ ሀገር በቀል ዛፎች መተከላቸውን ጠቅሰው፤ ሀገር በቀል የኮንሶ የአካባቢ ጥበቃ እውቀቶች አሻራ ያረፈበት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም አንስተዋል። መሰል የአካባቢ ጥበቃና ልማት ሥራዎች ኢትዮጵያ ተምሳሌታዊና ተጠቃሽ ሀገር እያደረጋት ነው ሲሉም ዋና ዳይሬክተሯ አመላከተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ እሸቱ ለማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የእግረኛ መንገዶች፣የሳይክልና አማራጭ መንገዶችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በተሽከርካሪዎች ወደ አየር የሚለቀቀውን በካይ ጋዝ እንዲቀንስ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል። ፕሮጀክቱ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ለውጤት በቅቷል ከዚህ በኋላ ፕሮጀክቱ በሚጠበቀው ደረጃ አገልግሎት እንዲሰጥ ሕዝቡ ሊንከባከበው ይገባል ብለዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ዶኤ (ዶ/ር)፤ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያዊያን አቅም በአጭር ጊዜ ተገንብቶ ለውጤት መብቃቱ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ላይ ላላት ቁርጠኝነት መሰል የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ምስክሮች ናቸው ያሉት ተወካዩ ተፈጥሮን ከዘመናዊነት ጋር አጣጥሞ መሄድ ያለውን ውጤት አመላካች ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር ያስችላል
Jun 5, 2026 1212
አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር የሚያስችል መሆኑን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን እና መሠረተ-ልማት ዲቪዚዮን ዳይሬክተር ሮበርት ሊሲንጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን በሚያሳልጡ በትራንስፖርት፣ ኢንዱስትሪ፣ ኃይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂዎች እና በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ነው፡፡ በዚህም በየዓመቱ ለነዳጅ የሚወጣውን ወጪ መቀነስና በታዳሽ ኃይል የሚመራ የትራንስፖርት ሥርዓት መገንባት የሚያስችል ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂና የትግበራ ዕቅድ ይፋ አድርጋለች፡፡ በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ኢኖቬሽን እና መሠረተ-ልማት ዲቪዚዮን ዳይሬክተር ሮበርት ሊሲንጌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂ ከዓለም አቀፍ የህግ ማዕቀፎች ጋር የተናበበ ነው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባ ነዳጅ ጥገኛ በመሆናቸው ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጭ እንደሚዳረጉ ገልጸው፤ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂና የትግበራ ዕቅድ ወጭን ከመቀነስ ባሻገር ለአስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ዋስትና ይሆናል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እያደረገች ያለችው ሽግግር የአየር ብክለትን በመቀነስ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት አጋዥ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር እስከ 2030 አዲስ ከሚመዘገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል 30 በመቶ የሚሆኑትን በሀገር ውስጥ ለማምረትና ለመገጣጠም ማቀዷ በአፍሪካውያን መካከል ያለውን የንግድ ትስስር ያጠናክራል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መጀመር ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚደረገውን ሽግግር ያሳልጣል ያሉት ዳይሬክተሩ፥ በአህጉሪቱ ያለውን የንግድ እሴት ሰንሰለት እንደሚያቀላጥፍም ገልጸዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 5428
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 5330
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 4162
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 4068
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 4168
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 4790
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው። መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል። በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል። ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል። በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል። በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ። በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 4383
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 4613
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Jun 7, 2026 1121
ባሳለፍነው ሳምንት … ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባሳለፍነው ሳምንት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተካሂዷል። ድምፅ ለመስጠት 54 ሚሊየን 57 ሺህ 861 መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማሳወቁ ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለመራጮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምርጫው ወቅት ድምጽ ስለሰጡ መራጮች ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ማገልገል መታደል መሆኑን ገልጸው፤ ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይህንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ ሲሉም አስገንዝበዋል። ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ሥራ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 22 ነጥብ 25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን ይሸፍናል። ይህ ፕሮጀክት የማይቆራረጥ የልማት ሥራችን ኅያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሀገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና 73 አባላት ከያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል። ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ከአኅጉራችን ነባራዊ ሁኔታና ተሞክሮ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ አፍሪካዊ ተቋማት ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የምርጫ ሂደታችንን ለመደገፍ በመላው ሀገሪቱ ታዛቢዎችን በማሰማራት የምርጫ ታዛቢ ልዑኩ ላደረገው ያልተቆጠበ ጥረት እውቅና እና አድናቆት እየሰጠን፤ የምልከታውን የተሟላ ውጤት እንጠብቃለን ሲሉም አመላክተዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻ ልማት፤ የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳን የያዘ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽንም፤ ከወንዞቹ ባሻገር እስከ 50 ሜትር የሚዘልቅ መሆኑን አስረድተዋል። የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን እና የንግድ ቦታዎችን ልማት ማካተቱን ጠቅሰው፤ ከተማዋን በእጅጉ የቀየረ ነው ብለዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን ገጽታ እና አገልግሎት ከማሻሻል ባለፈ በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስ እና በተያያዙ ዘርፎች ለብዙ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም አብራርተዋል። አብዛኛው ሥራ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች መቀረጹና መተግበሩ፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት እና በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው ዐቅም እያደገ መምጣቱን ያሳያል ነው ያሉት። ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎች እና ቆሻሻዎች የሚጣሉባቸው፣ በወንዝ ዳርቻዎች በሚኖሩ ማኅበረሰቦች ላይ የጎርፍ አደጋ ይጋርጡ የነበሩት እነዚህ አካባቢዎች፤ አሁን ላይ ወደ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ለሕይወት ምቹ ወደሆነ የከተማ ቦታነት እየተቀየሩ መሆኑንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ሁኔታም፤ የንግድ እና የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ከዚህ ቀደም ከነበረው ያልተናበበ ሥራ ተላቀው በጥናትና በጋራ ግብ ተባብሮ መሥራት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ስለመሆኑ አመላክተዋል። ይህ ፈጣን የልማት ሥራ አዲስ አበባን አረንጓዴ፣ ይበልጥ የተሳሰረች፣ በኢኮኖሚ ንቁ እና ሰውን ማዕከል ያደረገች ከተማ የማድረግ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ላይ መሰረት የተጣለበት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ
በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ …
Jun 3, 2026 2229
በዮሐንስ ደርበው በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር ሞላወርቅ አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በዓለምም ሆነ በሀገራችን አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው የደም ግፊት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በቆይታቸውም፤ ለደም ግፊት አጋላጭ ስለሆኑ ምክንያቶችና ሊደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄም እንዲሁም ከመድሃኒት አወሳሰድ ጋር በተያያዘ ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አቅርበዋል። · የደም ግፊት ምንድን ነው? ደም በደም ሥሮቻችን ሲያልፍ፤ የሚለካው መጠን “የደም ግፊት” እንደሚባል ዶክተር ሞላወርቅ ያስረዳሉ። የላይኛው (ሲስቶሊክ ወይም ከፍተኛው) የደም ግፊት መጠን ልብ በምትኮማተርበት ጊዜ ደም ወደ ደም ሥር ሲረጭ የሚለካው መሆኑንም ይገልጻሉ። የታችኛው (ዲያስቶሊክ ወይም ዝቅተኛው) የደም ግፊት መጠን ደግሞ ልብ ደም ለመቀበል ለአፍታ ዕረፍት በምታገኝበት ጊዜ የሚከሰት የግፊት ደረጃ መሆኑንም ይገልጻሉ። · የደም ግፊት ደረጃዎች እና ማስጠንቀቂያቸው ዶክተር ሞላወርቅ እንደሚሉት፤ የጤናማ ሰው የደም የግፊት መጠን 120 በ 80 እና በታች መሆን ይኖርበታል። በሌላ በኩል ግን ይላሉ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 የታችኛው ደግሞ ከ80 በታች ከሆነ “ከፍ ያለ ወይም የጨመረ የደም ግፊት ደረጃ” ይባላል። የላይኛው ከ130 እስከ 139 ወይም የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከሆነ ደግሞ “ደረጃ አንድ የደም ግፊት” እንደሚባል ያስረዳሉ። የላይኛው ከ140 በላይ ሲሆን እና የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ ደግሞ “ደረጃ ሁለት የደም ግፊት” እንደሚባል ነው የሚገልጹት። በሌላ በኩል “የከፋ የደም ግፊት ደረጃ” የሚባል እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም የላይኛው ከ180 በላይ እና የታችኛው ከ120 በላይ ሲሆን ነው በማለት ያብራራሉ። · ለደም ግፊት መጨመር መንስዔዎቹ ምንድን ናቸው? በዋናነት ሁለት ዓይነት የደም ግፊት መኖሩን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ ከፍተኛ የደም ግፊት እና መንስዔው የሚታወቅ የደም ግፊት መሆኑን አስረድተዋል። በዋናነት ወይም በአብዛኛው ከ90 እስከ 95 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ደም ግፊት የሚባለው መሆኑን ገልጸው፤ በርካታ መንስዔዎች ሊኖሩት እንደሚችሉ ቢገመትም ሁሉም በውል እንደማይታወቁ ያነሳሉ። ከበርካታ መንስዔዎቹ መካከልም፤ በቤተሰብ የሚወረስ (ተላላፊ)፣ አካባቢያዊ ምክንያቶች እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ የሚሉት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። የአኗኗር ዘይቤ ሲባልም፤ የአመጋገብ ሥርዓት በተለይም ጨው የበዛበት ምግብ፣ ክብደት መጨመር፣ አካባቢያዊ ሁኔታዎች (አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ)፣ የስኳር ታማሚ መሆን የሚሉት ይጠቀሳሉ ይላሉ። · ለደም ግፊት በተለይም እነማን ተጋላጭ ናቸው? ዕድሜ በጨመረ ቁጥር የደም ግፊት የመከሰት ዕድሉም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በዚህም መሠረት ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ይናገራሉ። እንዲም በቤተሰብ የደም ግፊት ኬዝ ያለባቸው ሰዎች፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒክ ግሩፕ) ለምሳሌ፡- በጥቁሮች (አፍሪካውያን)፣ በኤስያውያን፣ በደቡብ ኤስያውያን ላይ ከፍተኛ የደም ግፊት ሊከሰት እንደሚችል ይገልጻሉ። እንደ ዶክተር ሞላወርቅ ማብራሪያ፤ በአጠቃላይ አጋላጭ ምክንያቶች በሁለት ተከፍለው ሊታዩ ይችላሉ። አንደኛው፡- ልንከላከላቸው (ልንቀንሳቸው) የምንችላቸው መሆናቸውን በመግለጽ ይህም የአመጋገብ ሥርዓትን ማስተካከል፣ ክብደት መቀነስ፣ አልኮልና ሲጋራ ማቆም እና መሰል መሆናቸውን አብራርተዋል። ሁለተኛው፡- ልንከላከላቸው የማንችላቸው መሆናቸውን ገልጸው ይህም፤ የዕድሜ መጨመር፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒሲቲ) እና በቤተሰብ የሚተላለፍ የሚሉትን ጠቅሰዋል። · የደም ግፊትን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? የደም ግፊ ከተከሰተ መቆጣጠር እንጅ ማዳን እንደማይቻል ገልጸው፤ ከላይ እንደተጠቀሰው አስቀድሞ መከላከል ወይም ማዘግየት የሚቻል እና መከላከል የማይቻል የደም ግፊት ደረጃ መኖሩን አስረድተዋል። · የደም ግፊት በውል የሚታወቅ ምልክት አለው? የደም ግፊት ሲከሰት ምልክት እንደሌለው በማንሳት፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ “ዝምተኛው ገዳይ” እስከመባል መድረሱን ዶክተር ሞላወርቅ ያነሳሉ። ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ግን፤ በአንድ ወይም በሁለት የሰውነት አካል ላይ ችግር ሊደርስ እንደሚችል ከዚህም ሲያልፍ እስከ ሞት እንደሚያደርስ ይጠቅሳሉ። በተያያዘም፤ የራስ ምታት፣ የዐይን ብዥ ብዥ ማለት፣ ትንፋሽ ማጠር፣ የድካም ስሜት፣ አንገት የመያዝ ዓይነት ስሜቶች የደም ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ሊስተዋሉ የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል። አክለውም፤ በአብዛኛው በሕብረተሰቡ ላይ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርስና ድንገት በጨመረ ጊዜ፤ ለሞት፣ ለአደጋ፣ ለልብ ድካም፣ አጣዳፊ ለሆነ የልብ ህመም፣ በጭንቅላት ላይ የደም መፍሰስ፣ የኩላሊት ድክመት፣ በደም ሥሮች በአግባቡ ደም እንዳይተላለፍ ማድረግ፣ ለዐይነ ስውርነት መዳረግን ጨምሮ መሰል ጉዳቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝበዋል። · መድኃኒት አወሳሰድ ላይ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ ዶክተር ሞላወርቅ እንደገለጹት፤ አንድ ሰው ደም ግፊት እንዳለበት ከተነገረው በኋላ ሕክምናውም እንደ ደም ግፊቱ ደረጃ ይለያያል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 ከሆነ “የጨመረ ግፊት” ይባላል፤ እዚህ ላይ ሰውየው ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አመጋገቡን እንዲያስተካክል፣ ስፖርት እንዲሠራ፣ ክብደት እንዲቀንስ፣ ሱስ (ሲጋራ፣ አልኮል) እንዲቀንስ ክትትል ይደረጋል ብለዋል። ስለዚህ መድኃኒት ሳይጀምር የአኗኗር ዘይቤን በማስተካከል የደም ግፊቱን ሊቀንሰው (ሊቆጣጠረው) ይችላል ማለት ነው ሲሉም ይገልጻሉ። “ደረጃ አንድ ግፊት” የሚለው ላይ ከደረሱ ግን ሕክምና የሚጀምሩም የማይጀምሩም እንዳሉ ተናግረዋል። ይህም ማለት የላይኛው ከ130 እስከ 139 የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከደረሰ ሕክምና የሚጀምሩት የስኳር ህመም ያለባቸው፣ የስትሮክ ህመም ያለባቸው፣ ከልብና ደም ሥር የተገናኙ ህመሞች ያሉባቸው ከሆኑ ቢያንስ አንድ የግፊት መድኃኒት መጀመርና ክትትል ማድረግ አለባቸው ይላሉ። በሌላ በኩል ግን ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ ሰዎች “ደረጃ ሁለት ግፊት” ላይ ከደረሱ (የላይኛው ከ140 የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ) ሁሉም መድኃኒት መጀመር እንዳለባቸው በአጽንዖት ገልጸዋል። የሚጀምሩት መድኃኒትም አሁን ባለው በተሻሻለው የሕክምና ዘይቤ ሁለት መድኃኒቶች የሚጀምሩበት ሁኔታ እንዳለ ነው የሚያስረዱት። የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ግን ለሁሉም የግፊት ዓይነቶች መሠረት (የሚመከር) መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ መድኃኒት ጀምሬያለሁ ብሎ የአኗኗር ዘይቤው ላይ ቸልተኝነት ሊኖር እንደማይገባም ነው የሚመከሩት። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከግፊት ጋር በተያያዘ ወደ ሆስፒታል መጥተው የሚታከሙ ታካሚዎች አብዛኞቹ፤ ጀምረው ያቋረጡ፣ ለመጀመር ፍላጎት የሌላቸው፣ ቅድመ ምርመራ ባለማድረግ ምክንያት ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ የተጎዱ ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። ስለዚህ የግፊት መድኃኒት ከተጀመረ ሊቋረጥ እንደማይችል አስጠንቅቀዋል። በየጊዜው ክትትል ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በሂደት እንደ ግፊቱ ሁኔታ መድኃኒቶች ሊቀነሱም ሊጨመሩም እንደሚችሉ አመላክተዋል። · የመስፋፋት ደረጃ የዓለም ጤና ድርጅት በ2024 ያወጣውን መረጃ ዋቢ አድርገው፤ 1/3ኛው የዓለም ሕዝቦች በደም ግፊት እንደሚጠቁ ዶክተር ሞላወርቅ አንስተዋል። ከእነዚህ መካከልም፤ 7 ነጥብ 6 ሚሊየን ገደማው በአንድም በሌላም ምክንያት ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ጠቁመዋል። አብዛኞቹ የደም ግፊት ታማሚዎች ቁጥር የሚመዘገበው ደግሞ በመካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ሀገራችንን ያካትታል ሲሉ ገልጸዋል። በሀገራችን ደረጃም ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ባይኖሩም ከግፊት ጋር በተያያዘ በ2001 ላይ በ35 ሳይቶች የተጠኑ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከ21 እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ በደም ግፊት የሚጠቃ ነው ይላሉ። በአብዛኛው ደግሞ ከተማ ላይ እንደሚበዛ ጠቁመው፤ በተለይም አዲስ አበባ ላይ እስከ 30 በመቶ እንደሚደርስ የጥናቶቹ ውጤቶች ማመላከታቸውን ተናግረዋል። አብዛኞቹ ኬዞች ደግሞ ዕድሜያቸው ከፍ ያለ፣ ክብደታቸው የጨመረ፣ አልኮል እና ሲጋራ የሚጠቀሙ እና የስኳር ህመም ያለባቸው ሰዎች ጋር የሚገናኙ መሆናቸውን አስረድተዋል። እንደ ዓለም አቀፍ ደረጃም ኬዙ ካለባቸው መካከል ግማሽ ያህሉ ግፊት እንዳለባቸው እንኳን እንደማያውቁ ነው የሚገልጹት። ለግፊት ሕክምና ትክክለኛ ክትትል አድርገው ግፊታቸውን በአግባቡ የሚቆጣጠሩት ከ 5 ሰዎች 1 መሆኑንም ጥናቶች ያሳያሉ ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ በሀገራችን በሕብረተሰቡ ዘንድ ለደም ግፊት መለካት ኬዙ ከተገኘም የሕክምና ክትትል የማድረግ ሁኔታዎች ዝቅተኛ መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ሕብረተሰቡ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከአካል ጉዳት እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል ተገንዝቦ፤ የደም ግፊቱን የመለካት ልምምዱን ሊያዳብር እንደሚገባ ዶክተር ሞላወርቅ መክረዋል። በሌላ በኩል እንደ ሀገራችን ባሉ ሆስፒታሎች በጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ ወይም መቋረጥ (ስትሮክ) ካለባቸው ሰዎች ከ70 እስከ 85 በመቶው ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ የሚከሰት መሆኑን ገልጸው፤ ድንገተኛ ግፊት መጨመር ከልብ እና ከደም ሥሮች ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዓለምም ሆነ እንደ ሀገር አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንደኛው ግፊት መሆኑንም አረጋግጠዋል። ስለዚህ የደም ግፊትን መለካት፣ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል፣ ከሱስ መራቅ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር ለጤናማ ሕይወት ከፍተኛ ሚና እንዳለው መክረዋል።
ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 5358
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 3095
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 12263
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 6885
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 12658
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 11130
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 4168
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 5886
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !