ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የምስራቅ አፍሪካን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማፋጠን የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ማጎልበት ያስፈልጋል
May 18, 2026 60
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማፋጠን የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ማጎልበት እንደሚያስፈልግ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። በሶማሌ ክልል ርዕሰ መዲና ጅግጅጋ ከተማ በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ከፍተኛ ቀጣናዊ ፎረም እየተካሄደ ይገኛል። ’’ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀው ፎረም ቀጣናዊ መፍትሄዎች ለቀጣናዊ ችግሮች የሚለውን ዕሳቤ ማስተዋወቅ ዋና ዓላማው አድርጓል። ይህ መድረክ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል፣ በሶማሌ ክልል መንግስትና ሌሎች አጋር አካላት በጋራ ተዘጋጅቷል። በጅግጅጋ ከተማ በተዘጋጀው ፎረም ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መንግስታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ምሁራን፣ ባለድርሻ አካላትና ተጋባዠ እንግዶች ታድመዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ፎረሙ የጋራ ዓላማን በማሳካት ሰላማዊና የተረጋጋ መፃኢ ጊዜን ለመቅረፅ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ቀንድ በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አስፈላጊ ቀጣናዎች አንዱ ነው ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ ቀጣናውም የአህጉራት የገበያና ባህል ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች ድልድይ ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና መልክ ዓምድራዊ አቀማመጥና የህዝቦች ብዝኃ ትስስርም ከታሪኩ ጋር ተዳምሮ አስፈላጊነቱን እንዲጎላ ማድረጉን አስረድተዋል። በሁሉም መለኪያ ወርቃማ ፀጋ የታደለው ቀጣናም ግጭት፣ አለመተማመን፣ መፈናቀል፣ የፖለቲካ ደካማነት፣ የሰብዓዊ መብት ጫና እና የውጭ ተፅዕኖ መታየት እንደሌለበት አብራርተዋል። የአፍሪካ ቀንድ በችግርና ቀውስ መነጽር የሚታይበት አካሄድም ቀጣናውን ከትብብር ይልቅ የፉክክር መንደር ተደርጎ እንዲሳል ማድረጉን አንስተዋል። ይህ መለወጥ አለበት ያሉት አፈ ጉባኤው፤ የአፍሪካ ቀንድ የወደፊት ዕጣ ፋንታም በራስ አቅም እንጂ በውጭ አካላት ሊጻፍ እንደማይገባ አስገንዝበዋል። በዚህም የቀጣናውን ሀገራት ልማት፣ ሰላምና ደኅንነት ለማጠናከር የተቋማት፣ የማህበረሰቡ፣ የምሁራን፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሴቶችና ወጣቶችን ትብብር ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አፅንኦት ሰጥተዋል። ቀጣናዊ ወኪልነትን ለማረጋገጥም በራስ ማሰብ፣ መፍትሔ መፈለግ፣ አጋርነትን ማጠናከር፣ የዕርስ በዕርስ ትብብርና የጋራ ዕድሎችን በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዜጎች መቀረፅ እንዳለበት ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ አጋሮችም ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ቀጣናዊ የልማት፣ ክብርና ሉዓላዊነት፣ ሰላምና ደኅንነትን የሚያረጋግጥ ድጋፍ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። ዘላቂ ሰላም በምኞት ብቻ አይገነባም ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ ሰላም የሚገነባውም በጠንካራ ተቋማት፣ በፍትሐዊና አካታች ትብብርና የፖለቲካ አጋርነት እንዲሁም በማይቋረጥ ውይይት ነው ብለዋል። ሰላም በሕዝብ አመኔታና በተጠያቂ ተቋማት ላይ ሊመሠረት እንደሚገባ አፅንኦት የሰጡት አፈ ጉባዔው፤ ኢትዮጵያ ሰላማዊ፣ የተረጋጋና የተባበረ የአፍሪካ ቀንድ እንዲኖር ጥልቅ ፍላጎት እንዳላት አስገንዝበዋል። የኢትጵያ ሰላም፣ ልማት፣ ትብብርና ቀጣናዊ ተሳተፎም ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተሳሰረ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ትብብርን በማጠናከር ሰላም ልማትና ብልፅግናቸውን ለማረጋገጥ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አጋርነትን ማጎልበት እንዳለባቸው አንስተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሐመድ፤ የሶማሌ ክልላዊ መንግስት ይህንን የጂግጂጋ ፎረም በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ብልጽግናን ለማስፈን የሚያስችሉ መንገዶችን ለመቀየስ የሚረዳ ስልታዊ የውይይት መድረክ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቀዋል። ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ ደህንነቱ ያልተጠበቀ አካባቢ ተደርጎ ይቆጠር የነበረው ክልል ዛሬ ተለውጦ እንዲህ አይነት የውይይት እና የሰላም ፎረም ማስተናገዱ ራሱ የሚሰጠው ተምሳሌትነት እጅግ የላቀ ትርጉም አለው ሲሉ ገልጸዋል። ይህ ታላቅ ውይይት በጂግጂጋ ከተማ መካሄዱ ልዩ ትርጉም እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡
በክልሉ ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
May 18, 2026 42
ደብረ ማርቆስ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተመለከተ። በደብረ ማርቆስ ከተማ ከ230 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተገነባ የገበያ ማእከል ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል። በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማእረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳሃሉ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችሉ ምርታማነትን የማሳደግ፣ የግብይት ስርአቱን የማሳለጥ፣ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ የማገናኘትና ህገ ወጥ ደላሎች ላይ ቁጥጥር የማጠናከር ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በደብረ ማርቆስ ከተማ የተገነባው የገበያ ማእከል የጥረቱ አንድ አካል መሆኑን ጠቁመው ማእከሉ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ግብይቱን በማሳለጥ በኩል ሚናው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በዚህ በኩል እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም አስተዳደሩ በዘርፉ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ድጋፍ እንደሚደረግ አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በበኩላቸው፤ የገበያ ማእከሉ አምራቹና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመገበያየት የሚያስችል ነው ብለዋል። ማእከሉ ለከተማዋ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑንም አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ዮሴፍ መለሰ በበኩላቸው፤ የገበያ ማእከሉ ከ230 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተገነባ መሆኑን ተናግረዋል። ማእከሉ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች የሚገበያዩበት በመሆኑ ለሸማቹ ህብረተሰብ የሚያስገኘው ጥቅም ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። የገበያ ማእከሉ መገንባት የንግድ ስርአቱን ለማዘመን የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ያሉት ደግሞ የከተማው ንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሙሉጌታ አስረስ ናቸው። በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ በመደመር እሳቤ ቀጣናዊ አጋርነትን ለማጠናከር እየተጋች ነው
May 18, 2026 69
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በመደመር እሳቤ በቀጣናው አብሮነትን በማጎልበት፣ ዘላቂ ሰላምንና ብልጽግናን በማረጋገጥ ቀጣናዊ አጋርነትን ለማጠናከር እየተጋች እንደምትገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ። በቀጣናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገውና “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው ፎረም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የአፍሪካ ቀንድ የቀጣናውን የፖለቲካ፣ የጸጥታ እና የኢኮኖሚ ገጽታ የሚቀርጹ ውስብስብ እና እርስ በእርስ የተሳሰሩ ፈተናዎች የተጋረጡበት መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣናው የሚታዩት የድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ ስጋቶች፣ ሕገወጥ ንግድ፣ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሌሎች የሽግግር ጊዜያዊ ስጋቶች ሰላምን የሚያደፈርሱና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን የሚያውኩ ናቸው ብለዋል። እነዚህ ጫናዎች ተቋማዊ የቅንጅት ክፍተቶችን በማባባስ፣ ቀጣናው በጋራ ለመስራት እና ትርጉም ያለው የንግድና የኢኮኖሚ ትስስርን ወደ ፊት ለማራመድ ያለውን አቅም የሚገድቡ መሆናቸውን አብራርተዋል። ለዚህም መሰል ቀጣናዊ የጋራ ፎረሞችን ማካሄድ ከፍተኛ ወሳኝነት እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡ ዘላቂ ሰላምና የጋራ ብልፅግና ሊመጣ የሚችለው መፍትሄዎች የህዝቡን ነባራዊ ሁኔታ፣ እሴት እና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ነገሮች የሚያንፀባርቁ ሲሆኑ ብቻ ነው ብለዋል። በመሆኑም ተግዳሮቶችን ለመሻገር፤ ሀገር በቀል ዕውቀትን፣ የአካባቢ ባለቤትነትን እና በዐውደ-ጽሑፍ ላይ የተመሰረተ ችግር መፍቻን ቅድሚያ የሚሰጠውን አዲስ አስተሳሰብ መቀበል እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሀገር ውስጥ መፍትሄዎችን በቁርጠኝነት በመምራት ረገድ መሪነት አሳይታለች ብለዋል፡፡ አካሄዳችን አገራዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በመቅረጽ እና በአገር ውስጥ በመረጃ የተደገፈ ማሻሻያ ለማድረግ የዜጎች ሁሉን አቀፍ ተሳትፎ ላይ ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተተገበረው የመደመር እሳቤ መሰረት ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገቻቸው ሀገራዊ ሪፎርሞች የህዝቦችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሁሉን አቀፍ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይህም የተለያዩ አቅሞችን በማሰባሰብ የተደመረ አቅምን የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ አስተሳሰብ ቀጣናዊ አንድነትን በማጎልበት፣ ዘላቂ ሰላምን፣ ብልጽግናን እና ሰብዓዊ ክብርን በመደገፍ እውነተኛ ቀጣናዊ ትብብር እንዲኖር በማድረግ ዘላቂ አጋርነትን ያጠናክራል ብለዋል። ኢትዮጵያ እየተከተለችው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ማሻሻያ ለሀገራዊ ልማት ስትራቴጂና ለቀጣናዊ ብልፅግና ያላትን ሰፊ ራዕይ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ማሻሻያው የግሉን ዘርፍ በማነቃቃት ለሀገራዊ እድገት እና ለተረጋጋ የፋይናንስ አካሄድ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። እነዚህ ማሻሻያዎች የኢትዮጵያን የውስጥ ኢኮኖሚ ለመለወጥ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጣናዊ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ጠንካራ አስተዋፅኦ ለማድረግ ጭምር ያለሙ መሆናቸውን አስረድተዋል። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ሥርዓትን ማዘመን፣ የመንገድና የባቡር መስመሮችን ማስፋፋት፣ የወደብ ተደራሽነትን ማሻሻል፣ እንዲሁም ከጎረቤቶቿና ከድንበር አካባቢዋ የሚያገናኙ የትራንስፖርት ኮሪደሮችን ማጠናከርን ጨምሮ ለመሠረተ ልማት ትስስር ቅድሚያ ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች ብለዋል። ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገትን ለመደገፍ እንዲሁም የአካባቢያዊ እና የአለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነትን ለማሻሻል ንፁህ እና በተመጣጣኝ ዋጋ የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦትን በማስፋፋት የቀጣናውን የሃይል ፍላጎት በማሟላት ላይ ትገኛለች ብለዋል። በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ቀጣናዊ ፎረም እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡
መረጃ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት እና የመረጃና የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ነው
May 18, 2026 45
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦መረጃ ልክ እንደ ወርቅ ውድ የሀገር ሀብት ከመሆኑም ባለፈ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት እንዲሁም የመረጃና የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ሀገራዊ ጉባኤ ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል። በንግግራቸው እንዳነሱት፣ መረጃ ልክ እንደ ወርቅ ውድ የሀገር ሀብት ከመሆኑም ባለፈ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት እንዲሁም የመረጃና የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ከሌሎች በሚገኝ መረጃ ላይ ሙሉ ለሙሉ መደገፍ የፖሊሲ ነጻነትን የሚያሳጣና ትክክለኛነቱ የሚያጠራጥር በመሆኑ፣ የራስን መረጃ በሀገር ልጅ መሰብሰብና መተንተን ትልቅ ሀገራዊ ኩራትና ዋስትና መሆኑን ተናግረዋል። ለዚህም የዳታ ምንጮችን በማብዛትና እርስ በርስ በማነፃፀር የጠራና የዘመነ የመረጃ ሥርዓት መዘርጋት ለሀገር እድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል። በተጨማሪም ይህንን ጥራትና ተደራሽነት በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ ደግሞ በአሁኑ ወቅት የሰው ሰራሽ አስተውህሎት (AI) ቴክኖሎጂን በግልና በመንግስት ተቋማት ውስጥ በጥልቀት መጠቀም አስፈላጊ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተው መናገራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።
በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ትብብር ያስፈልጋል
May 18, 2026 94
አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፡-በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ቀጣናዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ላይ ያተኮረ ፎረም በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። ፎረሙ እየተካሄደ የሚገኘው “በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር” በሚል መሪ ሐሳብ ነው። ሚኒስትሩ በፎረሙ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ድንበር ተሻጋሪ የንግድና የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር የቀጣናችንን ውስብስብ የሰላምና ደኅንነት ፈተናዎች በዘላቂነት ለመፍታት ጉልኅ አስተዋጽዖ አለው ብለዋል። አክለውም፤በተጠናከረ የተቋማት ቅንጅት ንግድን በማሳለጥ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር መሥራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የቀጣናውን ዘመናት የተሻገሩ ችግሮች ለመፍታት የነበረውን የቅንጅት ክፍተት በመስበር፤ ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበና ትብብርን ማዕከል ያደረገ አዲስ የመፍትሔ አቅጣጫ መከተል እንደሚገባም አመላክተዋል። ኢትዮጵያ አካታች በሆነው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ በመሠረተ-ልማትና የኃይል ትስስር እንዲሁም በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናዊ ውኅደቱን ለማፋጠን በቁርጠኝነት እየሠራች እንደምትገኝም አረጋግጠዋል። የቀጣናችን ሰላምና መረጋጋት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ፤በጋራ መተማመን ላይ የተመሰረተና ለተግዳሮት የማይበገር ቀጣናን ለመገንባት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር እንዲሠሩ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ቀጣናዊ ትብብር፣ የላቀ የኢኮኖሚ ውኅደት እና በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ የተመሠረቱ መፍትሔዎች ሊተገበሩ እንደሚገባም አመላክተዋል። የአፍሪካ ቀንድ እርስ በርስ የተሳሰሩ የፖለቲካ፣የጸጥታና የኢኮኖሚ ተግዳሮቶች ያሉበት መሆኑን በማስገንዘብ፤ ለዚህ ደግሞ የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ እንደሚያስፈልግ በአጽንኦት ገልጸዋል። ድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ እጦት፣አክራሪነት፣ ሕገ-ወጥ ንግድ እና የተቋማት ቅንጅት መላላት በቀጣናው ዘላቂ መረጋጋትና የኢኮኖሚ እድገት ላይ እያሳደሩት የመጣውን ተጽዕኖም አንስተዋል በንግግራቸው። እንደ ዛሬው ፎረም ያሉ ተነሳሽነቶች በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ስትራቴጂካዊ ራስን የመቻል ዐቅምን ለመገንባት ለሚደረገው ውይይትና ትብብር ወሳኝ ዕድል እንደሚፈጥሩም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የፖለቲካ፣የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ተግዳሮቶችን ለመፍታት "ለሀገር በቀል መፍትሔዎች" የምትሰጠውን ትኩረት አረጋግጠው፤ለአብነትም በልዩነት ውስጥ አንድነትን እና የጋራ እድገት የሚያበረታታውን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀረበውን የ“መደመር” ፍልስፍና ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ዋና ትኩረት የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ማጠናከር፣ምርታማነትን ማሻሻል እና በግል ዘርፍ የሚመራ እድገትን ማሳደግ መሆኑን በመጠቆም፤በተመሳሳይ ጊዜ ሀገሪቱን የቀጣናው የኢኮኖሚ ውኅደት አንቀሳቃሽ ኃይል ማድረግ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በትራንስፖርት ኮሪደሮች፣በሎጅስቲክስ ዘመናዊነት፣በባቡር መስመር ዝርጋታ እና በወደብ ተደራሽነት ማሻሻያ ላይ ያደረገችውን የመሠረተ-ልማት ኢንቨስትመንት ጠቅሰው፤ ይህም ለቀጣናዊ ውኅደት ያለውን የጎላ ፋይዳ አብራርተዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ እድገትንና ቀጣናዊ ትስስርን ለመደገፍ ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ተመጣጣኝና ንጹህ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ረገድ እያደረገች ያለውን ቀጣናዊ የኃይል ኤክስፖርት ዕድገት አንስተዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና የኢኮኖሚ ትብብርን ለማስፈን ያላትን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል። ሰላማዊ፣የተቀናጀ እና በኢኮኖሚ ንቁ የሆነ ቀጣና ለመገንባት የጋራ መረዳዳት፣ የጋራ መተማመን እና ጠንካራ ቀጣናዊ አጋርነት አስፈላጊ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ፎረሙ እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቀጥል የወጣው መርሐ-ግብር ያስረዳል።
ፖለቲካ
የምስራቅ አፍሪካን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማፋጠን የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ማጎልበት ያስፈልጋል
May 18, 2026 60
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማፋጠን የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ማጎልበት እንደሚያስፈልግ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። በሶማሌ ክልል ርዕሰ መዲና ጅግጅጋ ከተማ በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ከፍተኛ ቀጣናዊ ፎረም እየተካሄደ ይገኛል። ’’ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀው ፎረም ቀጣናዊ መፍትሄዎች ለቀጣናዊ ችግሮች የሚለውን ዕሳቤ ማስተዋወቅ ዋና ዓላማው አድርጓል። ይህ መድረክ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል፣ በሶማሌ ክልል መንግስትና ሌሎች አጋር አካላት በጋራ ተዘጋጅቷል። በጅግጅጋ ከተማ በተዘጋጀው ፎረም ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መንግስታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ምሁራን፣ ባለድርሻ አካላትና ተጋባዠ እንግዶች ታድመዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ፎረሙ የጋራ ዓላማን በማሳካት ሰላማዊና የተረጋጋ መፃኢ ጊዜን ለመቅረፅ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ቀንድ በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አስፈላጊ ቀጣናዎች አንዱ ነው ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ ቀጣናውም የአህጉራት የገበያና ባህል ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች ድልድይ ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና መልክ ዓምድራዊ አቀማመጥና የህዝቦች ብዝኃ ትስስርም ከታሪኩ ጋር ተዳምሮ አስፈላጊነቱን እንዲጎላ ማድረጉን አስረድተዋል። በሁሉም መለኪያ ወርቃማ ፀጋ የታደለው ቀጣናም ግጭት፣ አለመተማመን፣ መፈናቀል፣ የፖለቲካ ደካማነት፣ የሰብዓዊ መብት ጫና እና የውጭ ተፅዕኖ መታየት እንደሌለበት አብራርተዋል። የአፍሪካ ቀንድ በችግርና ቀውስ መነጽር የሚታይበት አካሄድም ቀጣናውን ከትብብር ይልቅ የፉክክር መንደር ተደርጎ እንዲሳል ማድረጉን አንስተዋል። ይህ መለወጥ አለበት ያሉት አፈ ጉባኤው፤ የአፍሪካ ቀንድ የወደፊት ዕጣ ፋንታም በራስ አቅም እንጂ በውጭ አካላት ሊጻፍ እንደማይገባ አስገንዝበዋል። በዚህም የቀጣናውን ሀገራት ልማት፣ ሰላምና ደኅንነት ለማጠናከር የተቋማት፣ የማህበረሰቡ፣ የምሁራን፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሴቶችና ወጣቶችን ትብብር ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አፅንኦት ሰጥተዋል። ቀጣናዊ ወኪልነትን ለማረጋገጥም በራስ ማሰብ፣ መፍትሔ መፈለግ፣ አጋርነትን ማጠናከር፣ የዕርስ በዕርስ ትብብርና የጋራ ዕድሎችን በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዜጎች መቀረፅ እንዳለበት ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ አጋሮችም ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ቀጣናዊ የልማት፣ ክብርና ሉዓላዊነት፣ ሰላምና ደኅንነትን የሚያረጋግጥ ድጋፍ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። ዘላቂ ሰላም በምኞት ብቻ አይገነባም ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ ሰላም የሚገነባውም በጠንካራ ተቋማት፣ በፍትሐዊና አካታች ትብብርና የፖለቲካ አጋርነት እንዲሁም በማይቋረጥ ውይይት ነው ብለዋል። ሰላም በሕዝብ አመኔታና በተጠያቂ ተቋማት ላይ ሊመሠረት እንደሚገባ አፅንኦት የሰጡት አፈ ጉባዔው፤ ኢትዮጵያ ሰላማዊ፣ የተረጋጋና የተባበረ የአፍሪካ ቀንድ እንዲኖር ጥልቅ ፍላጎት እንዳላት አስገንዝበዋል። የኢትጵያ ሰላም፣ ልማት፣ ትብብርና ቀጣናዊ ተሳተፎም ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተሳሰረ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ትብብርን በማጠናከር ሰላም ልማትና ብልፅግናቸውን ለማረጋገጥ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አጋርነትን ማጎልበት እንዳለባቸው አንስተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሐመድ፤ የሶማሌ ክልላዊ መንግስት ይህንን የጂግጂጋ ፎረም በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ብልጽግናን ለማስፈን የሚያስችሉ መንገዶችን ለመቀየስ የሚረዳ ስልታዊ የውይይት መድረክ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቀዋል። ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ ደህንነቱ ያልተጠበቀ አካባቢ ተደርጎ ይቆጠር የነበረው ክልል ዛሬ ተለውጦ እንዲህ አይነት የውይይት እና የሰላም ፎረም ማስተናገዱ ራሱ የሚሰጠው ተምሳሌትነት እጅግ የላቀ ትርጉም አለው ሲሉ ገልጸዋል። ይህ ታላቅ ውይይት በጂግጂጋ ከተማ መካሄዱ ልዩ ትርጉም እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ በመደመር እሳቤ ቀጣናዊ አጋርነትን ለማጠናከር እየተጋች ነው
May 18, 2026 69
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በመደመር እሳቤ በቀጣናው አብሮነትን በማጎልበት፣ ዘላቂ ሰላምንና ብልጽግናን በማረጋገጥ ቀጣናዊ አጋርነትን ለማጠናከር እየተጋች እንደምትገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ። በቀጣናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገውና “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው ፎረም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የአፍሪካ ቀንድ የቀጣናውን የፖለቲካ፣ የጸጥታ እና የኢኮኖሚ ገጽታ የሚቀርጹ ውስብስብ እና እርስ በእርስ የተሳሰሩ ፈተናዎች የተጋረጡበት መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣናው የሚታዩት የድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ ስጋቶች፣ ሕገወጥ ንግድ፣ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሌሎች የሽግግር ጊዜያዊ ስጋቶች ሰላምን የሚያደፈርሱና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን የሚያውኩ ናቸው ብለዋል። እነዚህ ጫናዎች ተቋማዊ የቅንጅት ክፍተቶችን በማባባስ፣ ቀጣናው በጋራ ለመስራት እና ትርጉም ያለው የንግድና የኢኮኖሚ ትስስርን ወደ ፊት ለማራመድ ያለውን አቅም የሚገድቡ መሆናቸውን አብራርተዋል። ለዚህም መሰል ቀጣናዊ የጋራ ፎረሞችን ማካሄድ ከፍተኛ ወሳኝነት እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡ ዘላቂ ሰላምና የጋራ ብልፅግና ሊመጣ የሚችለው መፍትሄዎች የህዝቡን ነባራዊ ሁኔታ፣ እሴት እና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ነገሮች የሚያንፀባርቁ ሲሆኑ ብቻ ነው ብለዋል። በመሆኑም ተግዳሮቶችን ለመሻገር፤ ሀገር በቀል ዕውቀትን፣ የአካባቢ ባለቤትነትን እና በዐውደ-ጽሑፍ ላይ የተመሰረተ ችግር መፍቻን ቅድሚያ የሚሰጠውን አዲስ አስተሳሰብ መቀበል እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሀገር ውስጥ መፍትሄዎችን በቁርጠኝነት በመምራት ረገድ መሪነት አሳይታለች ብለዋል፡፡ አካሄዳችን አገራዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በመቅረጽ እና በአገር ውስጥ በመረጃ የተደገፈ ማሻሻያ ለማድረግ የዜጎች ሁሉን አቀፍ ተሳትፎ ላይ ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተተገበረው የመደመር እሳቤ መሰረት ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገቻቸው ሀገራዊ ሪፎርሞች የህዝቦችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሁሉን አቀፍ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይህም የተለያዩ አቅሞችን በማሰባሰብ የተደመረ አቅምን የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ አስተሳሰብ ቀጣናዊ አንድነትን በማጎልበት፣ ዘላቂ ሰላምን፣ ብልጽግናን እና ሰብዓዊ ክብርን በመደገፍ እውነተኛ ቀጣናዊ ትብብር እንዲኖር በማድረግ ዘላቂ አጋርነትን ያጠናክራል ብለዋል። ኢትዮጵያ እየተከተለችው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ማሻሻያ ለሀገራዊ ልማት ስትራቴጂና ለቀጣናዊ ብልፅግና ያላትን ሰፊ ራዕይ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ማሻሻያው የግሉን ዘርፍ በማነቃቃት ለሀገራዊ እድገት እና ለተረጋጋ የፋይናንስ አካሄድ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። እነዚህ ማሻሻያዎች የኢትዮጵያን የውስጥ ኢኮኖሚ ለመለወጥ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጣናዊ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ጠንካራ አስተዋፅኦ ለማድረግ ጭምር ያለሙ መሆናቸውን አስረድተዋል። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ሥርዓትን ማዘመን፣ የመንገድና የባቡር መስመሮችን ማስፋፋት፣ የወደብ ተደራሽነትን ማሻሻል፣ እንዲሁም ከጎረቤቶቿና ከድንበር አካባቢዋ የሚያገናኙ የትራንስፖርት ኮሪደሮችን ማጠናከርን ጨምሮ ለመሠረተ ልማት ትስስር ቅድሚያ ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች ብለዋል። ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገትን ለመደገፍ እንዲሁም የአካባቢያዊ እና የአለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነትን ለማሻሻል ንፁህ እና በተመጣጣኝ ዋጋ የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦትን በማስፋፋት የቀጣናውን የሃይል ፍላጎት በማሟላት ላይ ትገኛለች ብለዋል። በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ቀጣናዊ ፎረም እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡
በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ትብብር ያስፈልጋል
May 18, 2026 94
አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፡-በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ቀጣናዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ላይ ያተኮረ ፎረም በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። ፎረሙ እየተካሄደ የሚገኘው “በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር” በሚል መሪ ሐሳብ ነው። ሚኒስትሩ በፎረሙ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ድንበር ተሻጋሪ የንግድና የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር የቀጣናችንን ውስብስብ የሰላምና ደኅንነት ፈተናዎች በዘላቂነት ለመፍታት ጉልኅ አስተዋጽዖ አለው ብለዋል። አክለውም፤በተጠናከረ የተቋማት ቅንጅት ንግድን በማሳለጥ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር መሥራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የቀጣናውን ዘመናት የተሻገሩ ችግሮች ለመፍታት የነበረውን የቅንጅት ክፍተት በመስበር፤ ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበና ትብብርን ማዕከል ያደረገ አዲስ የመፍትሔ አቅጣጫ መከተል እንደሚገባም አመላክተዋል። ኢትዮጵያ አካታች በሆነው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ በመሠረተ-ልማትና የኃይል ትስስር እንዲሁም በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናዊ ውኅደቱን ለማፋጠን በቁርጠኝነት እየሠራች እንደምትገኝም አረጋግጠዋል። የቀጣናችን ሰላምና መረጋጋት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ፤በጋራ መተማመን ላይ የተመሰረተና ለተግዳሮት የማይበገር ቀጣናን ለመገንባት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር እንዲሠሩ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ቀጣናዊ ትብብር፣ የላቀ የኢኮኖሚ ውኅደት እና በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ የተመሠረቱ መፍትሔዎች ሊተገበሩ እንደሚገባም አመላክተዋል። የአፍሪካ ቀንድ እርስ በርስ የተሳሰሩ የፖለቲካ፣የጸጥታና የኢኮኖሚ ተግዳሮቶች ያሉበት መሆኑን በማስገንዘብ፤ ለዚህ ደግሞ የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ እንደሚያስፈልግ በአጽንኦት ገልጸዋል። ድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ እጦት፣አክራሪነት፣ ሕገ-ወጥ ንግድ እና የተቋማት ቅንጅት መላላት በቀጣናው ዘላቂ መረጋጋትና የኢኮኖሚ እድገት ላይ እያሳደሩት የመጣውን ተጽዕኖም አንስተዋል በንግግራቸው። እንደ ዛሬው ፎረም ያሉ ተነሳሽነቶች በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ስትራቴጂካዊ ራስን የመቻል ዐቅምን ለመገንባት ለሚደረገው ውይይትና ትብብር ወሳኝ ዕድል እንደሚፈጥሩም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የፖለቲካ፣የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ተግዳሮቶችን ለመፍታት "ለሀገር በቀል መፍትሔዎች" የምትሰጠውን ትኩረት አረጋግጠው፤ለአብነትም በልዩነት ውስጥ አንድነትን እና የጋራ እድገት የሚያበረታታውን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀረበውን የ“መደመር” ፍልስፍና ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ዋና ትኩረት የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ማጠናከር፣ምርታማነትን ማሻሻል እና በግል ዘርፍ የሚመራ እድገትን ማሳደግ መሆኑን በመጠቆም፤በተመሳሳይ ጊዜ ሀገሪቱን የቀጣናው የኢኮኖሚ ውኅደት አንቀሳቃሽ ኃይል ማድረግ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በትራንስፖርት ኮሪደሮች፣በሎጅስቲክስ ዘመናዊነት፣በባቡር መስመር ዝርጋታ እና በወደብ ተደራሽነት ማሻሻያ ላይ ያደረገችውን የመሠረተ-ልማት ኢንቨስትመንት ጠቅሰው፤ ይህም ለቀጣናዊ ውኅደት ያለውን የጎላ ፋይዳ አብራርተዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ እድገትንና ቀጣናዊ ትስስርን ለመደገፍ ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ተመጣጣኝና ንጹህ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ረገድ እያደረገች ያለውን ቀጣናዊ የኃይል ኤክስፖርት ዕድገት አንስተዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና የኢኮኖሚ ትብብርን ለማስፈን ያላትን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል። ሰላማዊ፣የተቀናጀ እና በኢኮኖሚ ንቁ የሆነ ቀጣና ለመገንባት የጋራ መረዳዳት፣ የጋራ መተማመን እና ጠንካራ ቀጣናዊ አጋርነት አስፈላጊ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ፎረሙ እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቀጥል የወጣው መርሐ-ግብር ያስረዳል።
የቀጣናው ዕጣ ፈንታ ላይነጣጠል የተሳሰረ ነው -ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
May 18, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦የቀጣናው ዕጣ ፈንታ በማይነጣጠል መልኩ የተሳሰረ ነው ሲሉ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለጹ። በቀጣናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ከፍተኛ ቀጣናዊ ፎረም በሶማሌ ክልል ርዕሰ መዲና ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ ፎረሙ የሚካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን፣ “ቀጣናዊ መፍትሄዎች ለቀጣናዊ ችግሮች” የሚለውን እሳቤ ማስተዋወቅ ዋና አላማው አድርጓል። ይህ መድረክ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት በጋራ የተዘጋጀ ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች እና የማህበረሰብ መሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ገልጸዋል። ቀጣናዊ እጣ ፈንታችን በጋራና በማይነጣጠል መልኩ የተሳሰረ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። ሁሉም አካል የሌላውን አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ መጋራቱ የማይቀር ነው ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ ችግሮችን በጋራ መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል። በሞቃዲሾ፣ በአዲስ አበባ፣ በጅቡቲና በኬንያ ያሉ ማህበረሰቦች የእርስ በእርስ የአስተሳሰብና የእውነታ ክፍተት ሊኖርባቸው እንደሚችል የገለጹት ዋና ፀሐፊው፣ ይህ መድረክ ክፍተቱን ለመሙላት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ ፎረም እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልፅነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑ በቀጣናው ያሉትን ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። የአፍሪካ ቀንድ ፈተናዎች በቀጣናው ምሁራንና መሪዎች እጅ መፈታት እንዳለባቸው የጠቆሙት ዋና ፀሐፊው፣ ከማሕበራዊ ሚዲያ ፕሮፓጋንዳ ይልቅ እውነተኛውና ፍሬያማው መፍትሄ የሚገኘው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ይህ የጅግጅጋው ፎረም መሪዎችና ምሁራን ሁሉንም ሀሳቦች ይዘው በመምጣት በግልፅ የሚወያዩበት፣ የሚስማሙበት ወይም በልዩነቶች ላይ የሚግባቡበት መድረክ መሆኑን አብራርተዋል። በመሆኑም በውይይቱ የሚገኙ ተጨባጭ ውጤቶችና መፍትሄዎች በቀጣይ ለሚቀረጸው የጋራ ጉዞ እጅግ ጠቃሚና መሰረታዊ ግብዓት እንደሚሆኑ አስገንዝበዋል። ለኢጋድ እንደ ቀጣናዊ ተቋም የምሁራን ቡድን ውይይትና የውይይቱ ውጤት በቀጣይ አብሮ ለሚቀረጸው የጋራ ጉዞ እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ መድረክ ቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ የሚያስቀምጥ ጉባኤ እንደሚሆን ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል። ለዚህ ታላቅ ቀጣናዊ መድረክ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
ፓርቲው በለውጡ ዓመታት የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማልማት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶችን አስመዝግቧል
May 18, 2026 134
አመያ፤ ግንቦት10/2018 (ኢዜአ)-ብልጽግና ፓርቲ በለውጡ ዓመታት እምቅ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማልማት በየዘርፉ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች ማስመዝገቡን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮንታ ዞን አመያ ከተማ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫን በማስመልከት የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ያሉ እምቅ የተፈጥሮ ጸጋዎች አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል ባለፉት ዓመታት በፓርቲው መሪነት በተከናወኑ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በፓርቲው የተነደፈው አገር በቀል የኢኮኖሚ እሳቤ በተለያዩ ዘርፎች እመርታዊ ስኬት ለማምጣት ማስቻሉንም ገልጸዋል። የክልሉን ሕዝቦች የሠላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፍትሐዊ በሆነ መንገድ በመመለስ ለሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ መሰረት መጣሉንም ተናግረዋል። በለውጡ ዓመታት ቀደም ሲል የተዘነጉ አካባቢዎችን ጭምር ፓርቲው የልማት ተጠቃሚ ማድረጉን ያመለከቱት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በዚህም የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት መሳደግ ተችሏል ብለዋል። በቀጣይም ህዝብን ፍትሃዊ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች እንዲጠናከሩ፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫው ህብረተሰቡ ድምጹን ለፓርቲው በመስጠት ከጎኑ እንዲቆም ጠይቀዋል። በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንዳሉት፣ ፓርቲው ፈተናዎችን ተቋቁሞ በአካባቢ ያሉ ፀጋዎችን ወደልማት በመቀየር አኩሪ ድል እያስመዘገበ ይገኛል። የክልሉ ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር ዴሞክራሲዊ ጥያቄም በለውጡ ዓመታት ምላሽ ማግኘቱን የገለጹት አቶ ፍቅሬ፣ የነበረው በክልል የመደራጀት ጥያቄ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በህዝቦች ንቁ ተሳትፎ እውን መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል። ብልጽግና የክልሉን ህዝብ የዘመናት የልማትና የማደግ ፍላጎት እውን ለማድረግ ፀጋዎችንና አቅሞችን አቀናጅቶ በመምራት መሰረታዊ ለውጥ ያመጣ ፓርቲ ነው ሲሉም ተናግረዋል ። በቀጣይም ፓርቲው በጠቅላላ ምርጫው የህዝብ ይሁንታን ካገኘ ላልተመለሱ የህዝብ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠው፣ ለዚህም ህዝቡ ድምጹን በመስጠት ከጎኑ እንዲቆም ጠይቀዋል። "ብልጽግና ፓርቲ ሁለንተናዊ እድገትን ለማረጋገጥ በትጋት እየሰራ ነው" ያሉት የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ፣ በዞኑ ትኩረት የተነፈጋቸው የተፈጥሮ ሀብቶች በፓርቲው መሪነት በአዲስ እይታ ወደልማት ገብተው እመርታዊ ለውጥ መጥቷል ብለዋል። ከዚህ ባለፈ ተጀምረው ያልተጠናቀቁና በይደር የቆዩ የመንገድ፣ የድልድይ፣ የውሃ፣ የጤናና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ነው የጠቀሱት። ከሰልፉ ታዳሚዎች መካከል ወይዘሮ ውድነሽ ዶኖቾ እና ወጣት ሺባባው ሞገስ እንደገለጹት ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት እንደሀገርም ሆነ እንደዞኑ በመሰረተልማት፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በቱሪዝም ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ የልማት ሥራዎችን አከናውኗል። በቀጣይም በፓርቲው መሪነት በሁሉም ዘርፎች የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ድጋፋቸውን ለመግለጽ በመርሀግብሩ ላይ እንደተገኙ ገልጸዋል።
በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ፎረም በጅግጅጋ እየተካሄደ ነው
May 18, 2026 122
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በቀጣናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ፎረም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ፎረሙ የሚካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል ሀሳብ ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች እና የማህበረሰብ መሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ቀጣናዊ መፍትሄዎች ለቀጣናዊ ችግሮች የሚል እሳቤን ማስተዋወቅ ዋና አላማው ያደረገው ፎረሙ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማእከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋሮች በጋራ የተዘጋጀ ነው። ቀጣናዊ ፎረሙ እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ምክንያታዊነት በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚከናወን የሰላም ግንባታ እና የምክክር ሂደት ዋነኛውን ሚና ይጫወታል
May 18, 2026 193
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018(ኢዜአ)፦ ምክንያታዊነት በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚከናወን የሰላም ግንባታ እና የምክክር ሂደት ዋነኛውን ሚና ይጫወታል ሲል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ገለጸ፡፡ ምክንያታዊነት በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት እንዴት እየተቃኘ ነው? ምክንያታዊነት በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚከናወን የሰላም ግንባታ እና የምክክር ሂደት ዋነኛውን ሚና ይጫወታል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በተቋቋመበት የመመስረቻ አዋጅ ላይ ምክንያታዊነት ከሀገራዊ ምክክሩ መርሆዎች አንዱ ተደርጎ መደንገጉ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ ፅንሰ-ሀሳቡ በምክክር ሂደት ውስጥ በምን መንገድ እየተተገበረ እንዳለ ማወቁ አስፈላጊ ነው፡፡ በሀገራዊ ምክክር ዓውድ ውስጥ ምክንያታዊነት ከስሜታዊነት፣ ከጥላቻ እና ከሃሳብ ግትርነት የፀዳ በአንፃሩ አመክንዮን እና ማስረጃን መሰረት ያደረገ ውይይቶችን ለማድረግ እና ውሳኔዎችን ለማሳለፍ የሚያግዝ ቁልፍ የሥነ-ምግባር መርህ ነው፡፡ ይህም ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ የጋራ መፍትሔን ለመፈለግ የሚያደርጉትን በጎ ጥረት ያጠናክራል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግ ምክንያታዊነት በሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ እንዴት ተፈፃሚ እንደሚሆን የሚከተሉት ሀሳቦች ያብራራሉ፡፡ 1/ አመክንዮን እና ማስረጃን መሰረት በማድረግ በዚህ ሂደት ዜጎች እና ባለድርሻ አካላት ከስሜታዊነት እና ጥላቻ በፀዳ አኳኋን በውይይቶች ላይ ተሳትፎን ያደርጋሉ፡፡ ይህም የምክክሩ ዓውድ ሰላማዊ እንዲሆን የማድረግ አቅሙ ከፍተኛ ነው፡፡ 2/ ገለልተኝነትን እና ፍትአዊነትን መሰረት በማድረግ ምክንያታዊ የሆነ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ሚዛናዊ የሆኑ ውይይቶች እንዲደረጉ ከማገዙም በላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ድምፆቻቸው በእኩልነት እንዲሰሙ በር ከፋች ነው፡፡ 3/ በሰው ልጆች እኩልነት ማመንን በማበረታታት በሀገራችን የሚደረጉ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች የሰው ልጆች በጋራ ችግሮቻቸው ላይ የሚወያዮባቸው እንደመሆናቸው መጠን የሰው ልጀችን እኩልነት እና ተፈጥሯዊ ማንነት በማክበር እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
የምርጫው ሂደት ፖሊሲና ፕሮግራሞችን በነጻነት ለማስተዋወቅ እድል ፈጥሯል
May 17, 2026 481
ሰቆጣ ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ፓርቲዎች ፖሊሲና ፕሮግራሞቻቸውን በነጻነት ለማስተዋወቅ እድል የፈጠረ መሆኑ ተመለከተ። ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፓርቲ በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በሰቆጣ ከተማ ለሚገኙ አባላቱና ደጋፊዎቹ ማኑፌስቶውንና እጩዎችን አስተዋውቋል። የጥምረቱ የምርጫና ፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊና የአገው ብሄራዊ ሸንጎ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ አላምረው ይርዳው እንደገለጹት፤ ጥምረቱ የብሄር ብሄረሰቦች ስብስብ በመሆኑ ለእኩልነት መከበር ይሰራል። ፓርቲው የብሄራዊ ጥቅም መከበርን ዋነኛ አላማው በማድረግ ለሰላምና ብሄራዊ መግባባት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ከዚህ ቀደም ከነበረው በተለየ መልኩ በነጻነት በመንቀሳቀስ የፓርቲያቸውን ፖሊሲና ፕሮግራም ለማስተዋወቅ እድል የፈጠረ መሆኑን አመልክተዋል። በመርሀ ግብሩ የተሳተፉ የፓርቲው አባላት በበኩላቸው ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲከናወን የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።
ፖለቲካ
የምስራቅ አፍሪካን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማፋጠን የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ማጎልበት ያስፈልጋል
May 18, 2026 60
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማፋጠን የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ማጎልበት እንደሚያስፈልግ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። በሶማሌ ክልል ርዕሰ መዲና ጅግጅጋ ከተማ በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ከፍተኛ ቀጣናዊ ፎረም እየተካሄደ ይገኛል። ’’ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀው ፎረም ቀጣናዊ መፍትሄዎች ለቀጣናዊ ችግሮች የሚለውን ዕሳቤ ማስተዋወቅ ዋና ዓላማው አድርጓል። ይህ መድረክ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል፣ በሶማሌ ክልል መንግስትና ሌሎች አጋር አካላት በጋራ ተዘጋጅቷል። በጅግጅጋ ከተማ በተዘጋጀው ፎረም ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መንግስታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ምሁራን፣ ባለድርሻ አካላትና ተጋባዠ እንግዶች ታድመዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ፎረሙ የጋራ ዓላማን በማሳካት ሰላማዊና የተረጋጋ መፃኢ ጊዜን ለመቅረፅ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ቀንድ በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አስፈላጊ ቀጣናዎች አንዱ ነው ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ ቀጣናውም የአህጉራት የገበያና ባህል ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች ድልድይ ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና መልክ ዓምድራዊ አቀማመጥና የህዝቦች ብዝኃ ትስስርም ከታሪኩ ጋር ተዳምሮ አስፈላጊነቱን እንዲጎላ ማድረጉን አስረድተዋል። በሁሉም መለኪያ ወርቃማ ፀጋ የታደለው ቀጣናም ግጭት፣ አለመተማመን፣ መፈናቀል፣ የፖለቲካ ደካማነት፣ የሰብዓዊ መብት ጫና እና የውጭ ተፅዕኖ መታየት እንደሌለበት አብራርተዋል። የአፍሪካ ቀንድ በችግርና ቀውስ መነጽር የሚታይበት አካሄድም ቀጣናውን ከትብብር ይልቅ የፉክክር መንደር ተደርጎ እንዲሳል ማድረጉን አንስተዋል። ይህ መለወጥ አለበት ያሉት አፈ ጉባኤው፤ የአፍሪካ ቀንድ የወደፊት ዕጣ ፋንታም በራስ አቅም እንጂ በውጭ አካላት ሊጻፍ እንደማይገባ አስገንዝበዋል። በዚህም የቀጣናውን ሀገራት ልማት፣ ሰላምና ደኅንነት ለማጠናከር የተቋማት፣ የማህበረሰቡ፣ የምሁራን፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሴቶችና ወጣቶችን ትብብር ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አፅንኦት ሰጥተዋል። ቀጣናዊ ወኪልነትን ለማረጋገጥም በራስ ማሰብ፣ መፍትሔ መፈለግ፣ አጋርነትን ማጠናከር፣ የዕርስ በዕርስ ትብብርና የጋራ ዕድሎችን በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዜጎች መቀረፅ እንዳለበት ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ አጋሮችም ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ቀጣናዊ የልማት፣ ክብርና ሉዓላዊነት፣ ሰላምና ደኅንነትን የሚያረጋግጥ ድጋፍ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። ዘላቂ ሰላም በምኞት ብቻ አይገነባም ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ ሰላም የሚገነባውም በጠንካራ ተቋማት፣ በፍትሐዊና አካታች ትብብርና የፖለቲካ አጋርነት እንዲሁም በማይቋረጥ ውይይት ነው ብለዋል። ሰላም በሕዝብ አመኔታና በተጠያቂ ተቋማት ላይ ሊመሠረት እንደሚገባ አፅንኦት የሰጡት አፈ ጉባዔው፤ ኢትዮጵያ ሰላማዊ፣ የተረጋጋና የተባበረ የአፍሪካ ቀንድ እንዲኖር ጥልቅ ፍላጎት እንዳላት አስገንዝበዋል። የኢትጵያ ሰላም፣ ልማት፣ ትብብርና ቀጣናዊ ተሳተፎም ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተሳሰረ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ትብብርን በማጠናከር ሰላም ልማትና ብልፅግናቸውን ለማረጋገጥ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አጋርነትን ማጎልበት እንዳለባቸው አንስተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሐመድ፤ የሶማሌ ክልላዊ መንግስት ይህንን የጂግጂጋ ፎረም በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ብልጽግናን ለማስፈን የሚያስችሉ መንገዶችን ለመቀየስ የሚረዳ ስልታዊ የውይይት መድረክ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቀዋል። ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ ደህንነቱ ያልተጠበቀ አካባቢ ተደርጎ ይቆጠር የነበረው ክልል ዛሬ ተለውጦ እንዲህ አይነት የውይይት እና የሰላም ፎረም ማስተናገዱ ራሱ የሚሰጠው ተምሳሌትነት እጅግ የላቀ ትርጉም አለው ሲሉ ገልጸዋል። ይህ ታላቅ ውይይት በጂግጂጋ ከተማ መካሄዱ ልዩ ትርጉም እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ በመደመር እሳቤ ቀጣናዊ አጋርነትን ለማጠናከር እየተጋች ነው
May 18, 2026 69
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በመደመር እሳቤ በቀጣናው አብሮነትን በማጎልበት፣ ዘላቂ ሰላምንና ብልጽግናን በማረጋገጥ ቀጣናዊ አጋርነትን ለማጠናከር እየተጋች እንደምትገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ። በቀጣናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገውና “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው ፎረም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የአፍሪካ ቀንድ የቀጣናውን የፖለቲካ፣ የጸጥታ እና የኢኮኖሚ ገጽታ የሚቀርጹ ውስብስብ እና እርስ በእርስ የተሳሰሩ ፈተናዎች የተጋረጡበት መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣናው የሚታዩት የድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ ስጋቶች፣ ሕገወጥ ንግድ፣ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሌሎች የሽግግር ጊዜያዊ ስጋቶች ሰላምን የሚያደፈርሱና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን የሚያውኩ ናቸው ብለዋል። እነዚህ ጫናዎች ተቋማዊ የቅንጅት ክፍተቶችን በማባባስ፣ ቀጣናው በጋራ ለመስራት እና ትርጉም ያለው የንግድና የኢኮኖሚ ትስስርን ወደ ፊት ለማራመድ ያለውን አቅም የሚገድቡ መሆናቸውን አብራርተዋል። ለዚህም መሰል ቀጣናዊ የጋራ ፎረሞችን ማካሄድ ከፍተኛ ወሳኝነት እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡ ዘላቂ ሰላምና የጋራ ብልፅግና ሊመጣ የሚችለው መፍትሄዎች የህዝቡን ነባራዊ ሁኔታ፣ እሴት እና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ነገሮች የሚያንፀባርቁ ሲሆኑ ብቻ ነው ብለዋል። በመሆኑም ተግዳሮቶችን ለመሻገር፤ ሀገር በቀል ዕውቀትን፣ የአካባቢ ባለቤትነትን እና በዐውደ-ጽሑፍ ላይ የተመሰረተ ችግር መፍቻን ቅድሚያ የሚሰጠውን አዲስ አስተሳሰብ መቀበል እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሀገር ውስጥ መፍትሄዎችን በቁርጠኝነት በመምራት ረገድ መሪነት አሳይታለች ብለዋል፡፡ አካሄዳችን አገራዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በመቅረጽ እና በአገር ውስጥ በመረጃ የተደገፈ ማሻሻያ ለማድረግ የዜጎች ሁሉን አቀፍ ተሳትፎ ላይ ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተተገበረው የመደመር እሳቤ መሰረት ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገቻቸው ሀገራዊ ሪፎርሞች የህዝቦችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሁሉን አቀፍ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይህም የተለያዩ አቅሞችን በማሰባሰብ የተደመረ አቅምን የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ አስተሳሰብ ቀጣናዊ አንድነትን በማጎልበት፣ ዘላቂ ሰላምን፣ ብልጽግናን እና ሰብዓዊ ክብርን በመደገፍ እውነተኛ ቀጣናዊ ትብብር እንዲኖር በማድረግ ዘላቂ አጋርነትን ያጠናክራል ብለዋል። ኢትዮጵያ እየተከተለችው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ማሻሻያ ለሀገራዊ ልማት ስትራቴጂና ለቀጣናዊ ብልፅግና ያላትን ሰፊ ራዕይ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ማሻሻያው የግሉን ዘርፍ በማነቃቃት ለሀገራዊ እድገት እና ለተረጋጋ የፋይናንስ አካሄድ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። እነዚህ ማሻሻያዎች የኢትዮጵያን የውስጥ ኢኮኖሚ ለመለወጥ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጣናዊ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ጠንካራ አስተዋፅኦ ለማድረግ ጭምር ያለሙ መሆናቸውን አስረድተዋል። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ሥርዓትን ማዘመን፣ የመንገድና የባቡር መስመሮችን ማስፋፋት፣ የወደብ ተደራሽነትን ማሻሻል፣ እንዲሁም ከጎረቤቶቿና ከድንበር አካባቢዋ የሚያገናኙ የትራንስፖርት ኮሪደሮችን ማጠናከርን ጨምሮ ለመሠረተ ልማት ትስስር ቅድሚያ ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች ብለዋል። ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገትን ለመደገፍ እንዲሁም የአካባቢያዊ እና የአለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነትን ለማሻሻል ንፁህ እና በተመጣጣኝ ዋጋ የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦትን በማስፋፋት የቀጣናውን የሃይል ፍላጎት በማሟላት ላይ ትገኛለች ብለዋል። በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ቀጣናዊ ፎረም እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡
በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ትብብር ያስፈልጋል
May 18, 2026 94
አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፡-በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ቀጣናዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ላይ ያተኮረ ፎረም በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። ፎረሙ እየተካሄደ የሚገኘው “በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር” በሚል መሪ ሐሳብ ነው። ሚኒስትሩ በፎረሙ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ድንበር ተሻጋሪ የንግድና የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር የቀጣናችንን ውስብስብ የሰላምና ደኅንነት ፈተናዎች በዘላቂነት ለመፍታት ጉልኅ አስተዋጽዖ አለው ብለዋል። አክለውም፤በተጠናከረ የተቋማት ቅንጅት ንግድን በማሳለጥ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር መሥራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የቀጣናውን ዘመናት የተሻገሩ ችግሮች ለመፍታት የነበረውን የቅንጅት ክፍተት በመስበር፤ ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበና ትብብርን ማዕከል ያደረገ አዲስ የመፍትሔ አቅጣጫ መከተል እንደሚገባም አመላክተዋል። ኢትዮጵያ አካታች በሆነው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ በመሠረተ-ልማትና የኃይል ትስስር እንዲሁም በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናዊ ውኅደቱን ለማፋጠን በቁርጠኝነት እየሠራች እንደምትገኝም አረጋግጠዋል። የቀጣናችን ሰላምና መረጋጋት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ፤በጋራ መተማመን ላይ የተመሰረተና ለተግዳሮት የማይበገር ቀጣናን ለመገንባት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር እንዲሠሩ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጠንካራ ቀጣናዊ ትብብር፣ የላቀ የኢኮኖሚ ውኅደት እና በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ የተመሠረቱ መፍትሔዎች ሊተገበሩ እንደሚገባም አመላክተዋል። የአፍሪካ ቀንድ እርስ በርስ የተሳሰሩ የፖለቲካ፣የጸጥታና የኢኮኖሚ ተግዳሮቶች ያሉበት መሆኑን በማስገንዘብ፤ ለዚህ ደግሞ የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ እንደሚያስፈልግ በአጽንኦት ገልጸዋል። ድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ እጦት፣አክራሪነት፣ ሕገ-ወጥ ንግድ እና የተቋማት ቅንጅት መላላት በቀጣናው ዘላቂ መረጋጋትና የኢኮኖሚ እድገት ላይ እያሳደሩት የመጣውን ተጽዕኖም አንስተዋል በንግግራቸው። እንደ ዛሬው ፎረም ያሉ ተነሳሽነቶች በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ስትራቴጂካዊ ራስን የመቻል ዐቅምን ለመገንባት ለሚደረገው ውይይትና ትብብር ወሳኝ ዕድል እንደሚፈጥሩም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የፖለቲካ፣የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ተግዳሮቶችን ለመፍታት "ለሀገር በቀል መፍትሔዎች" የምትሰጠውን ትኩረት አረጋግጠው፤ለአብነትም በልዩነት ውስጥ አንድነትን እና የጋራ እድገት የሚያበረታታውን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀረበውን የ“መደመር” ፍልስፍና ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ዋና ትኩረት የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ማጠናከር፣ምርታማነትን ማሻሻል እና በግል ዘርፍ የሚመራ እድገትን ማሳደግ መሆኑን በመጠቆም፤በተመሳሳይ ጊዜ ሀገሪቱን የቀጣናው የኢኮኖሚ ውኅደት አንቀሳቃሽ ኃይል ማድረግ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በትራንስፖርት ኮሪደሮች፣በሎጅስቲክስ ዘመናዊነት፣በባቡር መስመር ዝርጋታ እና በወደብ ተደራሽነት ማሻሻያ ላይ ያደረገችውን የመሠረተ-ልማት ኢንቨስትመንት ጠቅሰው፤ ይህም ለቀጣናዊ ውኅደት ያለውን የጎላ ፋይዳ አብራርተዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ እድገትንና ቀጣናዊ ትስስርን ለመደገፍ ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ተመጣጣኝና ንጹህ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ረገድ እያደረገች ያለውን ቀጣናዊ የኃይል ኤክስፖርት ዕድገት አንስተዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና የኢኮኖሚ ትብብርን ለማስፈን ያላትን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል። ሰላማዊ፣የተቀናጀ እና በኢኮኖሚ ንቁ የሆነ ቀጣና ለመገንባት የጋራ መረዳዳት፣ የጋራ መተማመን እና ጠንካራ ቀጣናዊ አጋርነት አስፈላጊ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ፎረሙ እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቀጥል የወጣው መርሐ-ግብር ያስረዳል።
የቀጣናው ዕጣ ፈንታ ላይነጣጠል የተሳሰረ ነው -ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
May 18, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦የቀጣናው ዕጣ ፈንታ በማይነጣጠል መልኩ የተሳሰረ ነው ሲሉ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለጹ። በቀጣናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ከፍተኛ ቀጣናዊ ፎረም በሶማሌ ክልል ርዕሰ መዲና ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ ፎረሙ የሚካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን፣ “ቀጣናዊ መፍትሄዎች ለቀጣናዊ ችግሮች” የሚለውን እሳቤ ማስተዋወቅ ዋና አላማው አድርጓል። ይህ መድረክ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት በጋራ የተዘጋጀ ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች እና የማህበረሰብ መሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ገልጸዋል። ቀጣናዊ እጣ ፈንታችን በጋራና በማይነጣጠል መልኩ የተሳሰረ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። ሁሉም አካል የሌላውን አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ መጋራቱ የማይቀር ነው ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ ችግሮችን በጋራ መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል። በሞቃዲሾ፣ በአዲስ አበባ፣ በጅቡቲና በኬንያ ያሉ ማህበረሰቦች የእርስ በእርስ የአስተሳሰብና የእውነታ ክፍተት ሊኖርባቸው እንደሚችል የገለጹት ዋና ፀሐፊው፣ ይህ መድረክ ክፍተቱን ለመሙላት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ ፎረም እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልፅነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑ በቀጣናው ያሉትን ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። የአፍሪካ ቀንድ ፈተናዎች በቀጣናው ምሁራንና መሪዎች እጅ መፈታት እንዳለባቸው የጠቆሙት ዋና ፀሐፊው፣ ከማሕበራዊ ሚዲያ ፕሮፓጋንዳ ይልቅ እውነተኛውና ፍሬያማው መፍትሄ የሚገኘው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ይህ የጅግጅጋው ፎረም መሪዎችና ምሁራን ሁሉንም ሀሳቦች ይዘው በመምጣት በግልፅ የሚወያዩበት፣ የሚስማሙበት ወይም በልዩነቶች ላይ የሚግባቡበት መድረክ መሆኑን አብራርተዋል። በመሆኑም በውይይቱ የሚገኙ ተጨባጭ ውጤቶችና መፍትሄዎች በቀጣይ ለሚቀረጸው የጋራ ጉዞ እጅግ ጠቃሚና መሰረታዊ ግብዓት እንደሚሆኑ አስገንዝበዋል። ለኢጋድ እንደ ቀጣናዊ ተቋም የምሁራን ቡድን ውይይትና የውይይቱ ውጤት በቀጣይ አብሮ ለሚቀረጸው የጋራ ጉዞ እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ መድረክ ቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ የሚያስቀምጥ ጉባኤ እንደሚሆን ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል። ለዚህ ታላቅ ቀጣናዊ መድረክ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
ፓርቲው በለውጡ ዓመታት የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማልማት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶችን አስመዝግቧል
May 18, 2026 134
አመያ፤ ግንቦት10/2018 (ኢዜአ)-ብልጽግና ፓርቲ በለውጡ ዓመታት እምቅ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማልማት በየዘርፉ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች ማስመዝገቡን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮንታ ዞን አመያ ከተማ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫን በማስመልከት የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ያሉ እምቅ የተፈጥሮ ጸጋዎች አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል ባለፉት ዓመታት በፓርቲው መሪነት በተከናወኑ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በፓርቲው የተነደፈው አገር በቀል የኢኮኖሚ እሳቤ በተለያዩ ዘርፎች እመርታዊ ስኬት ለማምጣት ማስቻሉንም ገልጸዋል። የክልሉን ሕዝቦች የሠላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፍትሐዊ በሆነ መንገድ በመመለስ ለሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ መሰረት መጣሉንም ተናግረዋል። በለውጡ ዓመታት ቀደም ሲል የተዘነጉ አካባቢዎችን ጭምር ፓርቲው የልማት ተጠቃሚ ማድረጉን ያመለከቱት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በዚህም የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት መሳደግ ተችሏል ብለዋል። በቀጣይም ህዝብን ፍትሃዊ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች እንዲጠናከሩ፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫው ህብረተሰቡ ድምጹን ለፓርቲው በመስጠት ከጎኑ እንዲቆም ጠይቀዋል። በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንዳሉት፣ ፓርቲው ፈተናዎችን ተቋቁሞ በአካባቢ ያሉ ፀጋዎችን ወደልማት በመቀየር አኩሪ ድል እያስመዘገበ ይገኛል። የክልሉ ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር ዴሞክራሲዊ ጥያቄም በለውጡ ዓመታት ምላሽ ማግኘቱን የገለጹት አቶ ፍቅሬ፣ የነበረው በክልል የመደራጀት ጥያቄ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በህዝቦች ንቁ ተሳትፎ እውን መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል። ብልጽግና የክልሉን ህዝብ የዘመናት የልማትና የማደግ ፍላጎት እውን ለማድረግ ፀጋዎችንና አቅሞችን አቀናጅቶ በመምራት መሰረታዊ ለውጥ ያመጣ ፓርቲ ነው ሲሉም ተናግረዋል ። በቀጣይም ፓርቲው በጠቅላላ ምርጫው የህዝብ ይሁንታን ካገኘ ላልተመለሱ የህዝብ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠው፣ ለዚህም ህዝቡ ድምጹን በመስጠት ከጎኑ እንዲቆም ጠይቀዋል። "ብልጽግና ፓርቲ ሁለንተናዊ እድገትን ለማረጋገጥ በትጋት እየሰራ ነው" ያሉት የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ፣ በዞኑ ትኩረት የተነፈጋቸው የተፈጥሮ ሀብቶች በፓርቲው መሪነት በአዲስ እይታ ወደልማት ገብተው እመርታዊ ለውጥ መጥቷል ብለዋል። ከዚህ ባለፈ ተጀምረው ያልተጠናቀቁና በይደር የቆዩ የመንገድ፣ የድልድይ፣ የውሃ፣ የጤናና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ነው የጠቀሱት። ከሰልፉ ታዳሚዎች መካከል ወይዘሮ ውድነሽ ዶኖቾ እና ወጣት ሺባባው ሞገስ እንደገለጹት ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት እንደሀገርም ሆነ እንደዞኑ በመሰረተልማት፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በቱሪዝም ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ የልማት ሥራዎችን አከናውኗል። በቀጣይም በፓርቲው መሪነት በሁሉም ዘርፎች የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ድጋፋቸውን ለመግለጽ በመርሀግብሩ ላይ እንደተገኙ ገልጸዋል።
በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ፎረም በጅግጅጋ እየተካሄደ ነው
May 18, 2026 122
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በቀጣናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ፎረም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ፎረሙ የሚካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል ሀሳብ ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች እና የማህበረሰብ መሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ቀጣናዊ መፍትሄዎች ለቀጣናዊ ችግሮች የሚል እሳቤን ማስተዋወቅ ዋና አላማው ያደረገው ፎረሙ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማእከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋሮች በጋራ የተዘጋጀ ነው። ቀጣናዊ ፎረሙ እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ምክንያታዊነት በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚከናወን የሰላም ግንባታ እና የምክክር ሂደት ዋነኛውን ሚና ይጫወታል
May 18, 2026 193
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018(ኢዜአ)፦ ምክንያታዊነት በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚከናወን የሰላም ግንባታ እና የምክክር ሂደት ዋነኛውን ሚና ይጫወታል ሲል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ገለጸ፡፡ ምክንያታዊነት በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት እንዴት እየተቃኘ ነው? ምክንያታዊነት በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚከናወን የሰላም ግንባታ እና የምክክር ሂደት ዋነኛውን ሚና ይጫወታል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በተቋቋመበት የመመስረቻ አዋጅ ላይ ምክንያታዊነት ከሀገራዊ ምክክሩ መርሆዎች አንዱ ተደርጎ መደንገጉ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ ፅንሰ-ሀሳቡ በምክክር ሂደት ውስጥ በምን መንገድ እየተተገበረ እንዳለ ማወቁ አስፈላጊ ነው፡፡ በሀገራዊ ምክክር ዓውድ ውስጥ ምክንያታዊነት ከስሜታዊነት፣ ከጥላቻ እና ከሃሳብ ግትርነት የፀዳ በአንፃሩ አመክንዮን እና ማስረጃን መሰረት ያደረገ ውይይቶችን ለማድረግ እና ውሳኔዎችን ለማሳለፍ የሚያግዝ ቁልፍ የሥነ-ምግባር መርህ ነው፡፡ ይህም ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ የጋራ መፍትሔን ለመፈለግ የሚያደርጉትን በጎ ጥረት ያጠናክራል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግ ምክንያታዊነት በሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ እንዴት ተፈፃሚ እንደሚሆን የሚከተሉት ሀሳቦች ያብራራሉ፡፡ 1/ አመክንዮን እና ማስረጃን መሰረት በማድረግ በዚህ ሂደት ዜጎች እና ባለድርሻ አካላት ከስሜታዊነት እና ጥላቻ በፀዳ አኳኋን በውይይቶች ላይ ተሳትፎን ያደርጋሉ፡፡ ይህም የምክክሩ ዓውድ ሰላማዊ እንዲሆን የማድረግ አቅሙ ከፍተኛ ነው፡፡ 2/ ገለልተኝነትን እና ፍትአዊነትን መሰረት በማድረግ ምክንያታዊ የሆነ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ሚዛናዊ የሆኑ ውይይቶች እንዲደረጉ ከማገዙም በላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ድምፆቻቸው በእኩልነት እንዲሰሙ በር ከፋች ነው፡፡ 3/ በሰው ልጆች እኩልነት ማመንን በማበረታታት በሀገራችን የሚደረጉ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች የሰው ልጆች በጋራ ችግሮቻቸው ላይ የሚወያዮባቸው እንደመሆናቸው መጠን የሰው ልጀችን እኩልነት እና ተፈጥሯዊ ማንነት በማክበር እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
የምርጫው ሂደት ፖሊሲና ፕሮግራሞችን በነጻነት ለማስተዋወቅ እድል ፈጥሯል
May 17, 2026 481
ሰቆጣ ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ፓርቲዎች ፖሊሲና ፕሮግራሞቻቸውን በነጻነት ለማስተዋወቅ እድል የፈጠረ መሆኑ ተመለከተ። ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፓርቲ በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በሰቆጣ ከተማ ለሚገኙ አባላቱና ደጋፊዎቹ ማኑፌስቶውንና እጩዎችን አስተዋውቋል። የጥምረቱ የምርጫና ፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊና የአገው ብሄራዊ ሸንጎ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ አላምረው ይርዳው እንደገለጹት፤ ጥምረቱ የብሄር ብሄረሰቦች ስብስብ በመሆኑ ለእኩልነት መከበር ይሰራል። ፓርቲው የብሄራዊ ጥቅም መከበርን ዋነኛ አላማው በማድረግ ለሰላምና ብሄራዊ መግባባት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ከዚህ ቀደም ከነበረው በተለየ መልኩ በነጻነት በመንቀሳቀስ የፓርቲያቸውን ፖሊሲና ፕሮግራም ለማስተዋወቅ እድል የፈጠረ መሆኑን አመልክተዋል። በመርሀ ግብሩ የተሳተፉ የፓርቲው አባላት በበኩላቸው ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲከናወን የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።
ማህበራዊ
መረጃ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት እና የመረጃና የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ነው
May 18, 2026 45
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦መረጃ ልክ እንደ ወርቅ ውድ የሀገር ሀብት ከመሆኑም ባለፈ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት እንዲሁም የመረጃና የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ሀገራዊ ጉባኤ ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል። በንግግራቸው እንዳነሱት፣ መረጃ ልክ እንደ ወርቅ ውድ የሀገር ሀብት ከመሆኑም ባለፈ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት እንዲሁም የመረጃና የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ከሌሎች በሚገኝ መረጃ ላይ ሙሉ ለሙሉ መደገፍ የፖሊሲ ነጻነትን የሚያሳጣና ትክክለኛነቱ የሚያጠራጥር በመሆኑ፣ የራስን መረጃ በሀገር ልጅ መሰብሰብና መተንተን ትልቅ ሀገራዊ ኩራትና ዋስትና መሆኑን ተናግረዋል። ለዚህም የዳታ ምንጮችን በማብዛትና እርስ በርስ በማነፃፀር የጠራና የዘመነ የመረጃ ሥርዓት መዘርጋት ለሀገር እድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል። በተጨማሪም ይህንን ጥራትና ተደራሽነት በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ ደግሞ በአሁኑ ወቅት የሰው ሰራሽ አስተውህሎት (AI) ቴክኖሎጂን በግልና በመንግስት ተቋማት ውስጥ በጥልቀት መጠቀም አስፈላጊ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተው መናገራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።
በአፍሪካ ቀንድ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለማለፍ የውይይት ባህልን ማጠናከር ያስፈልጋል
May 18, 2026 71
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለማለፍ ለአካታች ውይይቶች መጠናከር ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለጹ። በቀጣናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ፎረም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ፎረሙ የሚካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል ሀሳብ ነው። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) በፎረሙ ላይ እንደገለጹት በአፍሪካ ቀንድ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመሻገር ለአካታች ውይይት ቅድሚያ መስጠት እና ቀጣናዊ ህብረትን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የሀገራቱ እጣፋንታ በጋራ የተሳሰረ መሆኑን የገለጹት ዋና ፀሐፊው፤ ምሁራን በጋራ በመሆን ወሳኝ ጉዳዮች ላይ መወያየት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ ቀንድ ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉ በሀገራቱ ቅንጅት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያን፣ ሶማሊያን፣ ኬንያን፣ ጂቡቲንና ሌሎቹንም ሀገራት ያካተተ ውይይት በማድረግ በጋራ ጉዳዮች ላይ መተማመንን መፍጠር ይገባል ብለዋል። ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) ጠንካራ ኮሙኒኬሽንና ቀጣናዊ አካታችነትን ማጠናከርም የሚከሰቱ የሰላም ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚሰሩ ሥራዎች የአጋር አካላት ሚና የጎላ ነው
May 18, 2026 90
ጎንደር፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚሰሩ ሥራዎች የአጋር አካላት ሚና የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር ገለፀ። የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) በሰሜን፣ በምዕራብና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች በ186 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባቸውን የትምህርትና የጤና ተቋማት አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል። የልማት ማህበሩ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ማክሰኚት ከተማ ያስገነባው አንድ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የመማሪያ ክፍሎችን ነው ዛሬ ያስመረቀው። በምረቃው ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ፤ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚሰሩ ሥራዎች የአጋር አካላት ሚና የጎላ መሆኑን አንስተዋል። የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ሥራዎችን በማከናወን መንግስትን እያገዘና የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። በማህበሩ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ህዝቡ በገንዘብ፣ በቁሳቁስ፣ በጉልበቱና በእውቀቱ እንዲደግፍ የዞኑ መስተዳድር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። በዞኑ በርካታ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ፣ ፍጥነትና ጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁም ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ነው ያስታወቁት። በማህበሩ የጎንደር አካባቢ ልማት ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ዘውዴ እንደገለጹት፣ ማህበሩ በማህበራዊ ተቋማት ግንባታ ላይ አተኩሮ እየሰራ ነው። በዘንድሮው ዓመት በ186 ሚሊዮን ብር ወጪ በሦስቱ ዞኖች ያስገነባቸው 38 የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ገልጸዋል። ከእነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል ሁለቱ የጤና ኬላዎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ጎን ለጎን በ120 ሚሊዮን ብር ወጭ እየተገነቡ ያሉ 60 የትምህርትና የጤና ተቋማትን እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ለማጠናቀቅ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። ማህበረሰቡ ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ በጥሬ ገንዘብ 130 ሚሊዮን ብር አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመው፤ ተጨማሪ የአይነት፣ የጉልበትና የእውቀት አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል። የማክሰኚት ከተማ ነዋሪው አቶ ጥበቡ ዘለቀ ፤ አልማ ለህዝብ የሚሰራ የህዝብ የልማት ተቋም ነው ብለዋል። ልማት ማህበሩ በከተማው ለሚያስገነባቸው የትምህርት ተቋማት በገንዘብና በጉልበት በመደገፍ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውንም ተናግረዋል። የልማት ማህበሩ በሰሜን፣ በምዕራብና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች ከ600 ሺህ በላይ አባላትን በማፍራት የተለያዩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑም ታውቋል።
የደብረ ብርሃን ከተማን ለኢንዱስትሪ፣ ለኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ተመራጭ የማድረግ ተግባራት ይጠናከራሉ
May 18, 2026 84
ደብረ ብርሃን ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ብርሃን ከተማን ለኢንዱስትሪ፣ ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ተመራጭ የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ አስተዳደር ገለጸ። የከተማዋ አስተዳደር የልማት ተነሺ ለሆኑ አርሶ አደሮች ልጆች የቤት መሥሪያ ቦታ በማስረከብ ለዘመናት ሲነሳ የነበረውን ጥያቄ መፍታት መጀመሩንም አስታውቋል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት እንደገለፁት፤ የደብረ ብርሃን ከተማን ለኢንዱስትሪ፣ ለኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ተመራጭ የማድረግ ተግባራት ይጠናከራሉ። የከተማዋን የመሬት ስሪት በማዘመን ከተማዋን ለሁለንተናዊ ልማት ተመራጭ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በከተማዋ የተሳለጠ ልማትን እውን ለማድረግ ዘመናዊ የመሬት መረጃ አያያዝ ስርዓት ወደ ስራ መግባቱን ገልጸው ነዋሪውም ከልማቱ ተጠቃሚ የሚሆንበት አሰራር እየተተገበረ መሆኑን አክለዋል። በዚህም ለአርሶ አደሩ ተገቢውን ካሳ በመክፈል መሬቱን ለልማት በማዋል የከተማዋ እድገት እንዲፋጠን በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እድሜያቸው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ ለሆኑ የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች ልጆች የቤት መስሪያ ቦታ መስጠት በመቻሉ ለዘመናት ሲነሳ የነበረው የመልካም አስተዳደር ችግር መፈታቱን ጠቁመዋል። የቤት መገንቢያ ቦታ የተሰጣቸው በ18 ማህበራት ለተደራጁ 431 የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች ልጆች መሆናቸውን አስረድተዋል። ማህበራቱም በተረከቡት መሬት ላይ የከተማዋን ማስተር ፕላን በጠበቀ መልኩ የመኖሪያ ቤት ፈጥነው እንዲገነቡ አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የከተማ አስተዳደሩ መሬት መምሪያ ሃላፊ እታለማሁ ይምታቱ በበኩላቸው የከተማዋን የመሬት መረጃ አያያዝ በማዘመን ለኢንዱስትሪ፣ ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንትና ለመኖሪያ ቤት የማዋሉ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። የልማት ተነሺ ቤተሰቦች መሬታቸውን ለልማት በመልቀቅ ለከተማዋ እድገት መፋጠን አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ጠቁመዋል። ቦታ ከተረከቡ የልማት ተነሺ ልጆች መካከል ላቀው ሙሉጌታ፤ አስተዳደሩ በልማት ምክንያት ከመሬታቸው የሚነሱ አርሶ አደሮች ልጆችን ማየት በመጀመሩ ደስተኛ ነኝ ብሏል። በማህበር ተደራጅቶ 150 ሺህ ብር በመቆጠብ 150 ካሬ ሜትር የቤት መስሪያ ቦታ እንዳገኘም ወጣት ላቀው ተናግሯል።
ኢኮኖሚ
በክልሉ ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
May 18, 2026 42
ደብረ ማርቆስ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተመለከተ። በደብረ ማርቆስ ከተማ ከ230 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተገነባ የገበያ ማእከል ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል። በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማእረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳሃሉ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችሉ ምርታማነትን የማሳደግ፣ የግብይት ስርአቱን የማሳለጥ፣ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ የማገናኘትና ህገ ወጥ ደላሎች ላይ ቁጥጥር የማጠናከር ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በደብረ ማርቆስ ከተማ የተገነባው የገበያ ማእከል የጥረቱ አንድ አካል መሆኑን ጠቁመው ማእከሉ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ግብይቱን በማሳለጥ በኩል ሚናው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በዚህ በኩል እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም አስተዳደሩ በዘርፉ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ድጋፍ እንደሚደረግ አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በበኩላቸው፤ የገበያ ማእከሉ አምራቹና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመገበያየት የሚያስችል ነው ብለዋል። ማእከሉ ለከተማዋ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑንም አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ዮሴፍ መለሰ በበኩላቸው፤ የገበያ ማእከሉ ከ230 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተገነባ መሆኑን ተናግረዋል። ማእከሉ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች የሚገበያዩበት በመሆኑ ለሸማቹ ህብረተሰብ የሚያስገኘው ጥቅም ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። የገበያ ማእከሉ መገንባት የንግድ ስርአቱን ለማዘመን የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ያሉት ደግሞ የከተማው ንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሙሉጌታ አስረስ ናቸው። በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ ይቀጥላል-ተፎካካሪ ፓርቲዎች
May 18, 2026 76
ባህር ዳር፤ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ የሆነው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በፅኑ አቋም የምንሰራበት የጋራ አጀንዳችን ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ኢትዮጵያ የባህር መውጫ መግቢያ የተነፈጋት ሀገር ሆና መቀጠል የማትችልባቸው የተለያዩ አሳማኝ እውነታዎች ስለመኖራቸውም የፓርቲዎቹ አመራሮች አንስተዋል። በአንድ ወቅት የባህር በር ባለቤት የነበረችው ኢትዮጵያ ምክንያቱ በውል በማይታወቅ ሁኔታ ከባህር እንድትርቅና የተቆለፈባት ሀገር እንድትሆን ተደርጓል። ከቀይ ባህር በቅርብ ርቀት ላይ እያለች የኢፍትሃዊና ምክንያት አልባ በሆነ አግባብ ኢትዮጵያ ከባህር እንድትገለል የተደረገበት ጉዳይ የብዙ አመታት ቁጭት ቢሆንም አሁን ላይ ምላሽ የሚሻ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ መጥቷል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የፖለቲካም ይሁን ሌላ ልዩነት ሳይገድበው በጋራ የቆምንለት የሀገር ህልውና ጉዳይ ነው ሲሉ የፓርቲ አመራሮች ተናግረዋል። የአማራ ዲሞክራሲ ሃይሎች ንቅናቄ (አዴሃን) ስራ አስፈፃሚ አባል አዲሱ ጉልላት፤ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ጉዳይ በተቃርኖ ሊቆም የሚችል የፖለቲካ አቋም መኖር እንደሌለበት የጸና እምነት አለን ሲሉ ገልጸዋል። የሀገር ህልውና እና የብሄራዊ ጥቅም ጉዳይ የሆነው የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ መስራት የሁላችንም ግዴታ ነው ብለዋል። በመሆኑም የሀገር ህልውና እና የብሄራዊ ጥቅም ጉዳይ የሆነው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ መስራት የጋራ አጀንዳችን ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ምክትል ሊቀመንበር መልካሙ ፀጋየ፤ ፓርቲያቸው በሀገር ብሄራዊ ጥቅም ጉዳይ ወደ ኋላ ሳይል እየሰራ መሆኑንና በቀጣይም አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት ኢፍትሃዊነት ሁላችንም የምንቆጭበት በመሆኑ ለምላሹ ያለልዩነት በጋራ የምንሰራበት ታሪካዊ ምእራፍ ላይ እንገኛለን ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በታሪክ፣ በመልክአ ምድርም ይሁን በዓለም አቀፍ ህግ ተቀባይነት ያለው ፍትሃዊ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ የሆነው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በፅኑ አቋም የምንሰራበት የጋራ አጀንዳችን ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል። የኢትዮጰያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የሰሜን ኢትዮጵያ አስተባባሪ ሃይለማርያም ብርሃኑ፤ የባህር በር ለኢትዮጵያ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ፓርቲያቸው ይህንን ሀገራዊ የህልውና ጉዳይ በፅኑ አቋም አጀንዳው አድርጎ የሚሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ የሆነው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በዚህ ትውልድ ምላሽ ማግኘት ያለበት ብሄራዊ አጀንዳ መሆኑንም አጽኖት ሰጥተዋል።
በአማራ ክልል ሰላምን በማስጠበቅ ህብረተሰቡን የልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የተሰራው ስራ ውጤታማ ነው
May 18, 2026 98
ሐይቅ፤ ግንቦት 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰላምን በማስጠበቅ ህብረተሰቡን የልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የተሰራው ስራ ውጤት ማስገኘቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለፁ። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በምረቃው እንደገለፁት፣ የክልሉን ሰላም በማጽናት በተለያዩ አካባቢዎች በርካታ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል። በዚህም እንደ ሐይቅ ከተማ ያሉ በርካታ የቱሪዝም፣ የግብርና እና ሌሎች ፀጋዎች ያሏቸው ከተሞች የብልጽግና ጉዞ መጀመራቸው የሚበረታታ ነው ብለዋል። በከተማዋ በቅርቡ በገበታ ለትውልድ የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በአጭር ጊዜ የከተማዋንና የአካባቢውን ገጽታ በመቀየር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረጉን ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጭር ጊዜ ተገንብቶ ዛሬ የተመረቀው የኮሪደር ልማት ለከተማው ቱሪዝም ተጨማሪ የመስህብ አቅምና ውበትን የፈጠረ ነው ብለዋል። ህብረተሰቡ አንድነቱንና ሰላሙን በመጠበቅ የተጀመረውን ልማት በማስቀጠል ብልፅግናውን ለማረጋገጥ ከአካባቢው መስተዳድር ጋር ተባብሮ መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሊ መኮነን፣ በበኩላቸው ህብረተሰቡን በማሳተፍ የዞኑን ሰላም ማስጠበቅ በመቻሉ ለልማት ስራዎች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል። በዞኑ የተለያዩ ፕሮጀክቶች እየተገነቡና እየተመረቁ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ጠቁመው በሐይቅ ከተማ ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የኮሪደር ልማት የዚሁ ማሳያ ነው ያሉት። የኮሪደር ልማቱ ከሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጋር ተደምሮ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትን የፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ምቹ የመኖሪያ አካባቢን ለመፍጠርና ጎብኚዎችን ለመሳብ ያስችላል ብለዋል። የሐይቅ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ከድር መሀመድ በበኩላቸው፣ በከተማው በ130 ሚሊየን ብር የተገነባው ኮሪደር ልማት በአጭር ጊዜ በጥራት ተጠናቆ ለምረቃ መብቃቱን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማቱ የእግረኛና የሳይክል መንገድን ጨምሮ ሌሎችንም የመዝናኛ ስፍራዎች ያካተተ መሆኑን አብራርተዋል።
በኦሮሚያ ክልል በመኸር እርሻው 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በሩዝ ሰብል ይለማል
May 18, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በተያዘው የመኸር እርሻ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በሩዝ ሰብል እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሶ ፈይሳ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ክልሉ ለሩዝ ልማት ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በተሠራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት እየታየ ነው። በክልሉ በ2014/15 የምርት ዘመን በ100 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ተጀምሮ የነበረው የሩዝ ልማት፣ አሁን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ በማደግ የሕዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል። ይህ የሩዝ ልማት በተለይም በምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢ በሚገኙ ዞኖች በስፋት እየለማ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። ባለፈው ዓመት 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ ከለማው የሩዝ ሰብል ወደ 63 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን ጠቁመው በ2018/19 የምርት ዘመን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በማልማት 100 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል። በክልሉ በሩዝ ልማት ውጤታማ ለመሆን አመቺ የሆኑ አካባቢዎች በጥናት ተለይተው ኢኒሼቲቩ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት። አሁን ላይ ለአርሶ አደሩ የሚያስፈልገው ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በበቂ ሁኔታ የቀረበ ሲሆን፤ የባለሙያ የቅርብ ድጋፍና ክትትልም እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ከሩዝ ልማቱ አምራች አርሶ አደሮች የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መጥቷል ብለዋል። በልማቱ ዙሪያ የአርሶ አደሩ ተነሳሽነት በየጊዜው እያደገ የመጣ ሲሆን፤ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሰፋና አርሶ አደሩም በሩዝ ልማት ላይ የተሻለ ልምድ እያገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ለኒውክሊየር ኃይል ጣቢያ ግንባታ የሚሆን ምቹ አካባቢን በጥናት የመለየት ሥራ ተጀምሯል
May 18, 2026 136
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ለኒውክሊየር ኃይል ጣቢያ ግንባታ ምቹ አካባቢን በጥናት የመለየት ሥራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ከዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በኒውክሊየር ኃይል መገንቢያ ቦታ መስፈርቶችና ቅድመ ሁኔታዎች ላይ ትኩረት ያደረገ አውደ ጥናት እያካሄደ ይገኛል። ለአራት ቀናት በሚካሄደው በዚህ አውደ ጥናት ላይ ባለሙያዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው። የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ሽፈራው ተሊላ በወቅቱ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ያሉ እድገቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ አስተማማኝ እና ዘላቂ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ ነው። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በየዓመቱ 40 ቴራ ዋት አወር (TWh) ኃይል እንደሚያስፈልግ የገለጹት ምክትል ኮሚሽነሩ፤ በዚህም በሚቀጥሉት አስር ዓመታት ውስጥ የኃይል ፍላጎቱ ወደ 77 ቴራ ዋት አወር ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። በሀገሪቱ የኢንዱስትሪዎች መስፋፋት፣ የዲጂታል መሰረተ ልማት እንዲሁም የአገልግሎት ዘርፉ እያደገ መምጣት ከፍተኛ የኃይል አቅርቦት እንደሚጠይቅ ጠቅሰዋል፡፡ ይህንን የኃይል ፍላጎት በከፊል ከኒውክሊየር ኃይል ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ጋር በመተባበር የኒውክሊየር ኃይል ጣቢያ ለመገንባት የትኛው አካባቢ ምቹ እንደሆነ ለመለየት የሚያስችል ጥናት እያካሄደ መሆኑ ተገልጿል። በአሁኑ ወቅት የዳሰሳ ጥናቱ እየተጠናቀቀ መሆኑን የገለጹት አቶ ሽፈራው፤ በቀጣይ ይበልጥ ዝርዝር ጥናቶች ተደርገው ግንባታው የሚካሄድበት ትክክለኛ ቦታ መረጣ ይከናወናል ብለዋል። አሁን እየተካሄደ ያለው አውደ ጥናት ለቦታ መረጣው አስፈላጊ በሆኑ መስፈርቶችና አካሄዶች ላይ ጠቃሚ ግብዓት ለማግኘት እንደሚረዳም ጠቅሰዋል፡፡ በዘርፉ የሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና አስፈላጊ የሕግ ማዕቀፎችን ሥራ ላይ ለማዋል የዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አክለዋል፡፡ በዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ የኒውክሊየር ደህንነት ከፍተኛ ባለሙያ ሚካኤል ሳልሞን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይልን ለእድገት ማቀላጠፊያ መሳሪያ ለማድረግ ህልም ሰንቃ ጉዞ መጀመሯ ትልቅ ውሳኔ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ግንባታ እቅድ እንዲሳካ ኤጀንሲው አስፈላጊውን የቴክኒክና የሙያ ድጋፍ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብና መተንተን ወሳኝ ነው- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
May 18, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉዓላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችውን ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባኤና ኤግዚቢሽን ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በዘርፉ የተመለከቱት እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ እንዳገኙት ገልጸዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት እንደሆነ አስገንዝበዋል። ከሁሉም በላይ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች እውቀትና ክህሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት መሆኑን በመልዕክታቸው አንስተዋል። በተጨማሪም የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን እንዳለበትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ለሚመዘገበው ዕድገት መሠረት የሚሆን የሉዓላዊ ዲጂታል መሠረተ ልማት እየገነባች ነው
May 18, 2026 107
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ለሚመዘገበው ዕድገት መሠረት የሚሆን የሉዓላዊ ዲጂታል መሠረተ ልማት እየገነባች መሆኑን የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ገለጹ። ''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት'' በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ሀገራዊ ጉባኤ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ነው። በመድረኩ ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ለሚመዘገበው ዕድገት መሠረት የሚሆን የሉዓላዊ ዲጂታል መሠረተ ልማት እየገነባች ነው ብለዋል። እንደ ግብርና፣ ጤና፣ ፋይናንስ፣ ትምህርት እና ኢነርጂ ያሉ እያንዳንዱ ዘርፎች አሁን ላይ በሀገር በቀል የክላውድ ቴክኖሎጂ የሚቀነባበሩ፣ በሀገር ውስጥ የሚመሩ እና በኢትዮጵያ ቋንቋዎች መግባባት ለሚችለው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ግብዓት የሚሆኑ ተግባራዊ መረጃ ምንጮች ሆነዋል ነው ያሉት። የራሳችን መረጃ ከሌለን የኛ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ባዕድ ይሆናል፤ የራሳችን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ከሌለን ደግሞ መረጃዎቻችን ይባክናሉ ሲሉም አብራርተዋል። "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ይህንን ክፍተት ለመሙላት የተቀረጸ ብሔራዊ ስትራቴጂ ሲሆን፤ ይህም ሉዓላዊ የክላውድ ዳታ ሴንተርን፣ ብሔራዊ የዳታ ሌክ ሀውስን እንዲሁም በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ፣ በትግርኛ እና በሶማሊኛ ቋንቋዎች የሰለጠነ እና ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁጥጥር ስር የሚመራ ሀገር በቀል ላርጅ ላንግዌጅ ሞዴልን መገንባትን ያካትታል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀዳሚ እየሆኑ ያሉት ሀገራት መረጃቸውን ወደ ምርታማነትና ወደ አዲስ የኢኮኖሚ እሴት እየቀየሩ ያሉ ናቸው፤ ኢትዮጵያም አሁን ላይ ይህንኑ መሠረት እየገነባች ትገኛለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ የጥላቻ ንግግርና የተዛቡ መረጃዎችን ለመከላከል የሚደረገውን ቀጣናዊ ጥረት በግንባር ቀደምነት ትደግፋለች
May 18, 2026 94
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በዲጂታል ትስስር መስፋፋትና በሰው ሰራሽ አስተውሎ (AI) የሚታገዙ የጥላቻ ንግግሮችና የተዛቡ መረጃዎችን ለመከላከል በሚደረገው ቀጣናዊ ጥረት ኢትዮጵያ በግንባር ቀደምነት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍጹም ግርማ ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ በይነ-መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የጥላቻ ንግግርንና ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። የአፍሪካ ህብረት ተወካዮች፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢጋድ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ)፣ የመከላከያ ሚኒስቴር፣ የመገናኛ ብዙኃን (ሚዲያ) እንዲሁም የሙያ ማህበራት ተወካዮች በመድረኩ ላይ ተገኝተዋል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ፍጹም ግርማ እንደገለጹት፤ የዲጂታል መድረኮች መስፋፋትና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ መራቀቅ የጥላቻ ንግግሮችና የተዛቡ መረጃዎች ስጋትን ይበልጥ አጠናክሮታል። ኢትዮጵያ ይህንን ስጋት ለመግታት አገራዊ እርምጃዎችን በግንባር ቀደምትነት መውሰዷን ጠቅሰው ፤ በተለይም በጥላቻ ንግግሮችና በሀሰት መረጃዎች ላይ ግልጽ የወንጀል ተጠያቂነትን የደነገገውን "የጥላቻ ንግግር እና የሀሰት መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ" በምሳሌነት አንስተዋል። ሆኖም ግን አገር በቀል ጥረቶች ብቻቸውን በቂ እንዳልሆኑ ጠቁመው፤ የችግሩ ድንበር ተሻጋሪነት የጋራ ምላሽ የሚሻ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ድንበር ተሻጋሪ ስጋቶችን በብቸኝነት መከላከል ስለማይቻል የመንግስታት ትብብር፣ ቀጣናዊ ተቋማት፣ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ያካተተ የተቀናጀና ባለብዙ ወገን ምላሽ እንደሚያስፈልግ አፅንዖት ሰጥተዋል፡፡ ኢጋድ ይህንን የጋራ የመረጃ ስነ-ምህዳርን የማፅዳትና የቀጣናውን ሰላምና ማህበራዊ ትስስር የመጠበቅ ተነሳሽነት መውሰዱ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከኢጋድ፣ ከአፍሪካ ህብረት፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመሆን ስጋቶቹን ለመቆጣጠርና የቀጣናውን ሰላምና ብልፅግና ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል። የኢጋድ የግጭት ቅድመ-ማስጠንቀቂያና ምላሽ መስጫ ዳይሬክተር ካልሙስ ኦሞንጎ በበኩላቸው፤ መድረኩ የሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በተቀናጀ ሁኔታ የሚለዋወጡበት፣ በጋራ ወቅታዊ ሁኔታዎችን የሚገመግሙበትና ተያያዥ አደጋዎችን አስቀድመው የሚለዩበት ተግባራዊ የሥራ ትስስር እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ይህም ማኅበረሰብን የሚከፋፍሉ መረጃዎች ከመሰራጨታቸው በፊት አስቀድሞ የመለየት እና ተገቢውን ሕጋዊና ሙያዊ ምላሽ የመስጠት ሂደትን ያቀናጃል ሲሉ አብራርተዋል። የኢጋድ ሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ በበኩላቸው፤ የጥላቻ ንግግሮችና የተዛቡ መረጃዎች ድንበር ተሻጋሪ ስጋቶች ስለሆኑ የሁሉም አገራት ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በተለይ የመገናኛ ብዙኃን አካላት ግጭትን በመከላከል፣ እውነታን በማረጋገጥና ኃላፊነትን በመጠየቅ ረገድ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አስታውቀዋል። በመሆኑም ጋዜጠኞች መረጃዎችን በአግባቡ እንዲያረጋግጡ፣ አርታኢያን የዜና አቀራረብ ስልታቸውን በጥንቃቄ እንዲመርጡ እንዲሁም ተቋማት ደግሞ ግልጽና ወቅታዊ መረጃዎችን ለሚዲያ አካላት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። መድረኩ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
ስፖርት
የሊጉ መሪ አርሰናል ከበርንሌይ ጋር ይጫወታል
May 18, 2026 203
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት አርሰናል ከበርንሌይ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የሁለቱ ክለቦች መርሐ ግብር ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኤምሬትስ ስታዲየም ይካሄዳል። አርሰናል በ79 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ካሸነፈ ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ ያደርጋል። ጨዋታው ለመድፈኞቹ ዋንጫውን ለማንሳት እያደረጉት ባለው ጉዞ እጅጉን ወሳኝ የሚባል ነው። የሰሜን ለንደኑ ክለብ የዋንጫውን ዕድል ራሱ የመወሰን ዕድል አለው። ከሊጉ መውረዱ የተረጋገጠው በርንሌይ በ21 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዟል። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ አርሰናል 2 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የ45 ዓመቱ ፖል ቲርኒ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና 15 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ውድድሩን በሶስተኝነት አጠናቀቀች
May 18, 2026 134
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በጋና አክራ ከግንቦት 5 አንስቶ ሲካሄድ የቆየው 24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል። ኢትዮጵያ በአምስት ወርቅ፣ አራት የብር እና ስድስት የነሐስ በአጠቃላይ 15 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ውድድሩን ሶስተኛ በመሆን አጠናቃለች። በአህጉራዊው መድረክ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የገቡ አትሌቶች ባስመዘገቡት አንጸባራቂ ድል በኩራት የኢትዮጵያን ባንዲራ ከፍ ማድረግ መቻላቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በውድድሩ ከፍተኛውን ክብር ያገኙትና የወርቅ ሜዳሊያ ያሸነፉት አትሌቶች አትሌት አጃይባ አልዩ ፣ አትሌት ምስጋና ኃይሉ፣ አትሌት ገመቹ ጎዳና ፣አትሌት ምስጋናው ዋቁማ እና አትሌት ውብአለም ሽጉጤ ናቸው። የብር ሜዳሊያ ስኬት ያስመዘገቡት አትሌቶችና ቡድኖች ደግሞ የ4 በ 400 ሜትር የሴቶች ሪሌ ቡድን፣ አትሌት ኦታጌ ኦባንግ፣ አትሌት ሙቢን ሀጂ እና አትሌት ሀጎስ እዮብ መሆናቸው ታውቋል። በውድድሩ የነሐስና የክብር አሻራቸውን ያሳረፉት ቀሪዎቹ ስኬታማ አትሌቶች ደግሞ አትሌት አልማዝ ዮሐንስ፣ አትሌት ሳሙኤል ፍሬው፣ አትሌት ዘይን አየልኝ፣ አትሌት በፀሎት አለማየሁ፣ አትሌት አሰፉ አብርሃ እና አትሌት አብዱልሰላም አብዱልዋሂብ ናቸው። ኢትዮጵያ በዚህ በአህጉሪቱ የስፖርት መድረክ ላይ በ32 ሴት እና በ31 ወንድ አትሌቶች፣ በአጠቃላይ 63 አባላትን በመያዝ ጠንካራ ተሳትፎ አድርጋለች። የተመዘገበው ስኬት የኢትዮጵያን የአትሌቲክስ የበላይነት በአህጉሪቱ መድረክ ላይ ዳግም ያስመሰከረ መሆኑን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ኬንያ ስድስት የወርቅ፣ አራት የብር እና ሰባት የነሐስ በድምሩ 17 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቃለች። ደቡብ አፍሪካ በስድስት የወርቅ፣ ሁለት የብር እና ስድስት የነሐስ በድምሩ 12 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። ናይጄሪያ እና ኮትዲቭዋር አራተኛና አምስተኛ ደረጃን ይዘዋል። በሻምፒዮናው ላይ ከተሳተፉ ሀገራት መካከል 25ቱ የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ ገብተዋል። ኢትዮጵያ በካሜሮን ዱዋላ በተደረገው 23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአምስት የወርቅ፣ አራት የብር እና አንድ የነሃስ በድምሩ 10 ሜዳሊያዎችን በማግኘት አራተኛ መውጣቷ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በዘንድሮው ሻምፒዮና የሜዳሊያ ብዛት እና ደረጃዋን አሻሽላለች።
በወራጅ ቀጠና የሚገኘው ዌስትሃም ዩናይትድ በኒውካስትል ዩናይትድ ተሸነፈ
May 17, 2026 319
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኒውካስትል ዩናይትድ ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በሴንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዊሊያም ኦሱላ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኒክ ዎልትማደ ቀሪዋን ጎል ለኒውካስትል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ቫለንቲን ካስቴላኖስ ለዌስትሃም የማስተዛዘኛውን ጎል አስቆጥሯል። ባለሜዳው ኒውካስትል ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል። በሊጉ 14ኛ ድሉን ያስመዘገበው ኒውካስትል ዩናይትድ በ49 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 19ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ዌስትሃም ዩናይትድ በ36 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። የለንደኑ ክለብ በሊጉ የመቆየት ተስፋው ተመናምኗል። ማክሰኞ ቶተንሃም ቼልሲን ካሸነፈ ዌስትሃም ወደ ሻምፒዮንሺፑ ይወርዳል። ዛሬ በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ ኖቲንግሃም ፎረስትን 3 ለ 2 በማሸነፍ በ68 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ መጨረሱን አረጋግጧል። ሰንደርላንድ ኤቨርተንን 3 ለ 1፣ ሊድስ ዩናይትድ ብራይተንን 1 ለ 0 አሸንፈዋል። ብሬንትፎርድ ከክሪስታል ፓላስ ሁለት አቻ ሲለያዩ ፉልሃም እና ዎልቭስ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቋል። የ37ኛ ሳምንት ነገም ቀጥሎ ሲውል የሊጉ መሪ አርሰናል ከበርንሌይ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ከነገ በስቲያ ቦርንማውዝ ከማንችስተር ሲቲ እና ቼልሲ ከቶተንሃም ሆትስፐርስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለ6ኛ ተከታታይ ዓመት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ሆነ
May 17, 2026 211
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመቱ የመጨረሻ ጨዋታ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ መካከል ተከናውኗል። በዚህም መሠረት፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በእሙሽ ዳንኤል እና ረድዔት አስረሳኸኝ ግቦች ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎም፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለ6ኛ ተከታታይ ዓመት በአጠቃላይ ለ9ኛ ጊዜ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ሆኗል። ቀደም ብሎ በተከናወነ የዕለቱ መርሐ-ግብር መቻል እና አዲስ አበባ ከተማ 2 አቻ ተለያይተዋል። ይህን ተከትሎም መቻል በ56 ነጥብ 3ኛ ደረጃን ይዞ የውድድር ዓመቱን ሲያጠናቅቅ፤ በ16 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አዲስ አበባ ከተማ ወደ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ወርዷል።
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ጉዳት እያከመ ለመሆኑ የሀሮማያ ሐይቅ ህያው ማሳያ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
May 18, 2026 125
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ጉዳት እያከመ ለመሆኑ የሀሮማያ ሐይቅ ህያው ማሳያ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የሀሮማያ ሐይቅ ዳግም መወለድ አረንጓዴ አሻራ ከሰጠን ፍሬዎች አንዱ ነው ብለዋል። በ1996 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የነበረው የሀሮማያ ሐይቅ፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጥረት ዛሬ ወደ ቀደመ ውበትና ሥሪቱ ተመልሷል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አረንጓዴ አሻራን ለኢትዮጵያ የውሃ አካላትና ለተፋሰስ ልማት ቁልፍ ኢኒሼቲቭነቱን በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል። ይህ ስኬት በመደመር እሳቤ ልማትን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የተፈጥሮን ጫና መቋቋም እና መግራት እንደሚቻል ማረጋገጫ ነው ሲሉም አክለዋል። በአካባቢው ስንደርስ ለተደረገልን አቀባበል ምስጋና አቀርባለሁ ነው ያሉት በመልዕክታቸው።
ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት አስተማማኝና ወቅታዊ የአየር ንብረት መረጃ ማጠናከር ይገባል
May 18, 2026 85
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018(ኢዜአ)፦ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት ስኬት አስተማማኝ፣ ጥራት ያለውና ወቅታዊ የአየር ንብረት መረጃን በጋራ ማጠናከርና ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፈጠነ ተሾመ ተናገሩ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት( ኢጋድ) የአየር ጠባይ ትንበያ ማዕከል ጋር በመተባበር 73ኛውን የምስራቅ አፍሪካ የአየር ጸባይ አዝማሚያ ትንተናና ትንበያ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በፎረሙ ላይ የምስራቅ አፍሪካ አገራት ተወካዮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና የአለም ዓቀፍ ድርጅቶት ተወካዮች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፈጠነ ተሾመ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና በአየር ንብረት መለዋወጥና ተያያዥ የተፈጥሮ አደጋዎች ተጋላጭ በመሆኑ፣ ይህንን ተፅዕኖ ለመቋቋም አስተማማኝ የመረጃ ልውውጥ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ተፅዕኖ ለመቋቋም በርካታ አገራዊ ስራዎችን እያከናወነች እንደሚገኝም አብራርተዋል። ከእርምጃዎች መካከል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርንና የአየር ትንባያ ትንተናዎች የሚቲዎሮሎጂ ትንበያን ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገኙበት አንስተዋል። በዚህም ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን ነው የተናገሩት። የአየር ትንበያ ትንተናዎችን ይበልጥ ትክክለኛና ተአማኒ ለማድረግ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በጥቅም ላይ ማዋል መቻሉን ዋና ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል። ለቀጠናዊ ዘላቂ ልማት አስተማማኝና ወቅታዊ የአየር ንብረት መረጃ ማጠናከር እንደሚገባ አመላክተዋል። የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና በተደጋጋሚ ለድርቅ፣ ለድንገተኛ ጎርፍና ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ መጋለጡ የጋራ ስጋት መሆኑ በፎረሙ ላይ ተነስቷል። በመሆኑም አገራቱ በየግል ከሚያደርጉት ጥረት ባለፈ፣ በቀጠና ደረጃ ወጥ የሆነና ሳይንሳዊ መረጃን መሰረት ያደረገ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ስራ ላይ ማዋል ይገባቸዋል ብለዋል። የአየር ንብረት መረጃዎችን ማጠናከር አርሶ አደሮች፣ እንስሳት አርቢዎችና የፖሊሲ አውጪዎች አስቀድመው ውሳኔ እንዲያሳልፉና በልማት እቅዶች ላይ ዘላቂነት እንዲያረጋግጡ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልፅዋል። ፎረሙ ነገም ቀጥሎ እንደሚውል ተመላክቷል።
በኦሮሚያ ክልል 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የተፋሰስ ልማት ስራ ተከናውኗል
May 18, 2026 152
አዳማ ፤ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ የበጋ ወቅት 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የተፋሰስ ልማት ስራ መከናወኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ። በቢሮው የደን ልማትና ተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ ዳይሬክተር አቶ ከተማ አብዲሳ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ ባለፉት አመታት በተከናወነ የተፋሰስ ልማት ስራ የተራቆቱ አካባቢዎች አገግመዋል። የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ እረገድም አበረታች ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። ተሞክሮውን አጠናክሮ በማስቀጠል በዘንድሮ በጋ ወቅት 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ልማቱ መካሄዱን ተናግረዋል። በተፋሰስ ልማት ስራው የጋራና ማሳ ላይ እርከንና ክትር ጨምሮ የተለያዩ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል ። የተፋሰስ ልማት ስራ በተከናወነባቸው ስፍራዎች ላይ በክረምት ወቅት የችግኝ ተከላ ለማካሄድ የጉድጓድ ቁፋሮና ሌሎች ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን አመልክተዋል። በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የተፋሰስ ልማት ስራ የአፈር መሸርሸርና የጎርፍ ተጋላጭነትን በመቀነስ የመሬት ለምነት በመጨመሩ የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻሉን ጠቅሰዋል። የተራቆቱ አካባቢዎች በማገገማቸው ለሰብል ልማት አመች የሆነ ዝናብና እርጥበት እንዲኖር ማስቻሉን ጠቁመው የገፀ ምድርና የከርሰምድር የውሃ ሀብት በመጨመሩም የመስኖ ልማት በስፋት እንዲካሄድ አመቺ ሁኔታ መፈጠሩን አመልክተዋል። ባገገሙ ተፋሰሶች ላይ የእንስሳት መኖና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም የንብ ማነብ ስራዎች በማካሄድ ለስራ እድል ፈጠራ አይነተኛ ሚና መጫወቱንም ጠቅሰዋል ። የደረቁ ወንዞች፣ ጅረቶችና ሃይቆች ተመልሰው ለሰውና እንስሳት መጠጥ ውሀ ምንጭነት እንዲሁም ለአሳ እርባታና ለሌሎች አገልግሎቶች እንዲውሉ በማስቻል እረገድ ከፍተኛ አስተዋጾ ማድረጉን አስታውቀዋል ።
ቀጣናዊው የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም በአዲስ አበባ
May 18, 2026 136
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2018 (ኢዜአ)፡- 73ኛው የታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም (GHACOF 73) ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ይጀመራል። ፎረሙ የሚካሄደው “የአየር ንብረት አገልግሎቶች፤ ለአይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና የመተግበሪያ ማዕከል(ICPAC) ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን ፎረሙን እንዳዘጋጀው ተገልጿል። ስብሰባው ትንበያ ከመስጠት ባለፈ ትንበያዎቹን ወደ ተግባር መቀየር እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የቅድመ ማስጠንቀቂያና ቅድመ ዝግጅት እርምጃዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። የአየር ንብረት መረጃዎች አርሶ አደሮች፣ የጤና ባለሙያዎችንና የአደጋ ስጋት አመራሮችን በቀጥታ እንዲደግፉ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። በብሔራዊ የሚቲዎሮሎጂ ተቋማት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር ሌላኛው የመወያያ አጀንዳ ነው። መድረኩ ለታላቁ የአፍሪካ ቀንድ ግብርና እና የውሃ ሀብት ወሳኝ የሆነውን ከእ.አ.አ ከጁን እስከ ሴፕቴምበር 2026 ያለውን የዝናብ ወቅት ትንበያ ይቀርብበታል። ሚኒስትሮች፣ የምርምር ተቋማት፣ ሰብአዊ ድርጅቶች፣ የሲቪክ ማህበራት እና የግል ባለሀብቶች ይሳተፋሉ። ይህ የተሳታፊዎች ስብጥር ሳይንስን ከፖሊሲ ጋር ለማገናኘት የታለመ ነው። የአየር ንብረት መዛባት የሩቅ ስጋት መሆኑ ቀርቶ በደጃፋችን ላይ ያለ ተጨባጭ አደጋ ነው ያለው ኢጋድ ፎረሙ በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የሚገኙ ማህበረሰቦች በቂ መረጃ እንዲኖራቸውና አስቀድመው ዝግጁ እንዲሆኑ ማስቻል ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን አመልክቷል። በፎረሙ ማብቂያ የጋራ አቋም መግለጫ ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል። የጋራ መግለጫው በቀጣይ ለሚከናወኑ የቅድመ-ማስጠንቀቂያ ተግባራትና ለማህበረሰብ ጥንካሬ ግንባታ ስራዎች እንደ ዋና ግብዓት እንደሚያገለግል ተመላክቷል። ከዋናው መድረክ አስቀድሞ ከባለድርሻ አካላት ጋር የበይነ መረብ ውይይት እና የአየር ንብረት ትንበያ ልማት አውደ ጥናት ተደርጓል። ቀጣናዊ ፎረሙ እስከ ነገ ይቆያል። 72ኛው የታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም (GHACOF 72) በጥር ወር 2018 ዓ.ም በኬንያ ናይሮቢ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 948
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 645
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 569
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በአዲስ አበባ ይካሄዳል
May 13, 2026 607
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በሕብረቱ ዋና መቀመጫ ዛሬ በአዲስ አበባ ይደረጋል። በውይይቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እንደሚገኙ ይጠበቃል። ውይይቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል በአፍሪካ ልማት እና በዓለም አቀፍ አስተዳደር ዙሪያ ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ቅንጅት፣ የጋራ ተጠያቂነት እና ትብብርን በልማት፣ በአስተዳደር፣ በሰብአዊ ድጋፍ እና በሰላም ግንባታ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ያላቸውን ትስስር ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ይካሄዳል። በዚህ የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ላይ በርካታ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች የሚዳሰሱ ሲሆን፣ በተለይም የአጀንዳ 2063 እና የሁለተኛው የአስር ዓመት ምዕራፍ የትግበራ ዕቅድ አፈፃፀምን ማፋጠን እንዲሁም አፍሪካን በዓለም አቀፍ ፖሊሲ እና አስተዳደር ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና መጠበቅ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል። በተጨማሪም "ከጥገኝነት ወደ ሉዓላዊነት" የተሸጋገረ የልማት ፋይናንስ፣ የ2026 የአፍሪካ ሕብረት የዓመቱ መሪ ቃል የሆነው ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና የንጽህና አጠባበቅ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ተቋማት ሪፎርም እና አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ያላትን ውክልና የተመለከቱ ጉዳዮች ውይይት ይደረግባቸዋል። መድረኩ ለአህጉራዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔዎችን ማምጣት፣ የአገር ውስጥ ሀብት ማሰባሰብን ማሳደግ፣ የወጣቶች እና የሴቶች ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዲሁም በአህጉራዊ እና በዓለም አቀፍ የልማት የቅድሚያ ትኩረቶች መካከል ያለውን ትስስር ማጠናከር ወሳኝ መሆኑ አጽንኦት የሚሰጥበት እንደሆነ ተመላክቷል። ከውይይቱ ከሚጠበቁ ውጤቶች መካከል የተሻለ ስትራቴጂካዊ ቅንጅት፣ ፍትሐዊ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ፣ በአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ቃል ዙሪያ ጠንካራ ቅንጅት መፍጠር እና በተባበሩት መንግሥታት ሥርዓት ውስጥ ፍትሐዊ የአፍሪካ ውክልና እንዲኖር የቀረቡ ጥሪዎችን ማጠናከር እንደሚገኙበት ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የውይይቱን ውጤቶች አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ይሰጣሉ።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 282
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 1206
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 1030
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች
May 3, 2026 1106
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር እያሸጋገራት ይገኛል።የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የመሰረተ ልማት እና የተቋማት ግንባታ ስራዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋንኛ ስራዎች ናቸው። ለውጡን ተከትሎ መንግስት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን ስትራቴጂ በመቅረጽ የዲጂታላይዜሽን ስራውን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶ አድርጎታል። የለውጡ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ ቴክኖሎጂን እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመቁጠር "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን አጠቃላይ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ተግባር ገባ።ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱን የዲጂታል ጉዞ ከመሰረቱ የለወጠ ሲሆን፣የመጀመሪያው ትልቅ እርምጃም የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ነበር። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ የኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል።በተለይም የአምስተኛ ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን አስችሏታል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ለውጡ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ውጤት አምጥቷል።እንደ ቴሌብር (telebirr) ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ምንም የባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ፣ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር ትልቅ መደላድል ፈጥረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ አድማስ ይበልጥ አስፍተውታል። የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ራዕይ ለዓለም ያሳየችበት አጋጣሚ ነው።ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የካንሰር ህመምንና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ መለየት የሚያስችሉ የኤአይ ውጤቶችን አበልጽጓል። በግብርናውም ረገድ የአፈርን ለምነትና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ዋስትና ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል ዓለም ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የፋይዳ (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን መረጃ በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የለውጡ ፍሬያማነት ማሳያ ነው።የሳይንስ ሙዚየምም የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያሳይና የሀገሪቱን ቴክኖሎጂ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ሆኗል።የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቅርቡ መጠናቀቁ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2025 ስትራቴጂው መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዲጂታል 2030ን ይፋ ሲያደርጉ የነበረው ትልቁ መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች የሚል ነው። ስትራቴጂው በዋናነት"የፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት፣ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠር፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) አድርጎ መገንባትን እንደ ዋነኛ ግብ አስቀምጧል። ይህም ሁሉን አቀፍ የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ የመንግስት አገልግሎቶችን መቶ በመቶ ወረቀት አልባ በማድረግ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) በግብርና፣ በጤናና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ በስፋት በመተግበር የምርታማነት አብዮት መፍጠርን ያለመ ነው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ስራ በአህጉራዊ ደረጃ ያለውን ተቀባይነትና የተሰጣትን ትልቅ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት የቴክኖሎጂ ከፍታ፣ ሀገሪቱን በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ተፎካካሪ ብቻ ሳይሆን የፈጠራ ምንጭ እንድትሆንም እያደረጋት ይገኛል። በዚህ ረገድም የቀጣዩ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ስኬትም ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና በቴክኖሎጂ የበለጸገች ሀገር የማድረግ ራዕይን ለማሳካት እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ ያገለግላል።
ትንታኔዎች
እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት
May 17, 2026 2615
በኢዜአ ዐይን …! በዮሐንስ ደርበው እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉን የሚሉ እሮሮዎች በተለያዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሲነሱ ቆይተዋል። በተለይም በአንዳንድ ተቋማት መንግሥታዊ አገልግሎት ለማግኘት እዚያም እዚህም መንከራተት፤ደግሞም ወረፋ በመጠበቅ መጉላላት ብሎም ለጊዜና ገንዘብ ወጪ መዳረግ ይስተዋላል የሚሉ ሐሳቦች ተስተጋብተዋል። ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ባሳለፍነው ሳምንት … መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል አሠራር በመንደፍ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ አስጀመረ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማዕከሉ አገልግሎት ባስጀመሩበት ወቅትም ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው ብለው ነበር። አሁን ላይም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ነው።መስፋፋቱም በማዕከላት ብዛት፣በአገልግሎት መስጫ መስኮቶች ቁጥር እና በአገልግሎት ዐይነቶች እየተገለጠ ነው። በዚህም በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት የተደራጁ ሲሆን ይህ አሃዝም ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እና ያለውን ፈጣን እድገት ያመላክታል። ጉዳዩ የዜጎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ማላቅ፤ ብልሹ አሠራርንም መቅረፍ ነውና መንግሥት በልዩ ትኩረት ይዞታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ አሥተዳደርና በሐረሪ ክልል ጉብኝት ባደረጉበት ወቅትም፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የምልከታቸው አካል ማድረጋቸው ለጉዳዩ የተሰጠውን ከፍያለ ትኩረት ያሳያል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሶብ የሞባይል አገልግሎትን በመረቁበት ወቅት ደግሞ፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ብለዋል። አክለውም፤በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች ዕርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል፤ ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፤ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ መሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል ማለቱም ይታወቃል። የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ደግሞ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ ያስቻለ ስኬት ተገኝቷል ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ የመንግሥት አገልግሎቶችም ዜጋ ተኮር፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አብራርተዋል። በዲጂታል 2030 የአገልግሎት አሰጣጥ አመላካች ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚጠቀሱ 50 ሀገራት መካከል አንዷ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ዜጎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በኦንላይን በየትኛውም ቦታ ሁሉንም አገልግሎቶች እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ ስለመሆኑም እንዲሁ። አገልገሎቱን ያገኙ አስተያየት ሰጭዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ እንግልትን ያስቀረ፣ ጊዜና ወጭን የቀነሰ ነውና ይስፋፋ፤ ተጠናክሮም ይቀጥል። #መሶብ_የአንድ_ማዕከል_አገልግሎት #የዜጎችን_እንግልትና_ብልሹአሠራርን_መቅረፍ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #በኢዜአ_ዐይን
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 17, 2026 1305
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 2 እስከ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ጋር መምከራቸው ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም በኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል። ለነበረን ጠቃሚ የሐሳብ ልውውጥና ቀጣይነት ላለው አጋርነትም ምስጋናዬ የላቀ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ በኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና በፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በጋራ አዘጋጅነት በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካፍለዋል። በዚሁ ወቅትም በተለይም የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት እና የኃይል ሽግግርን በተመለከተው ውይይት ላይ ከተሞክሯችን የተቀዱ ከፍ ያሉ ሐሳቦች ተነስተዋል ብለዋል። አክለውም፤ ኢትዮጵያ በተነሱት ሁለት ዘርፎች የጀመረችውን ሥራ በማጠናከር የላቀ ሚና መጫወቷን ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንኳን ደህና መጡ ስል ሁልጊዜም በልዩ ኩራትና ደስታ ነው ሲሉ ተቀብለዋቸዋል። ከአቀባበሉ በኋላም፤ መሪዎች በጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በዚህም መሠረት፤ በታዳሽ፣ የተቀናጀ እና ዘላቂ ኃይል እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራምን ለመተግበር የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ ብድርን ጨምሮ የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የመንግሥትና የግል አጋርነት አዲስ የማዕቀፍ እና የፍኖተ ካርታ ስምምነት ተፈርሟል። · ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ማውጣቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርገዋል። እነዚህ አራት ቴምብሮች እ.ኤ.አ. በ1945 በሳን ፍራንሲስኮ የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን ከመፈረም ጀምሮ፤ በኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን እስከማሰማራት እና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ እስከ ማስተናገድ ያለውን የጋራ ታሪካችንን የሚተርኩ ናቸው ብለዋል። በዓለም የፖስታ ኅብረት በኩል ለ192 ሀገራት የተሰራጩት እነዚህ ቴምብሮች፤ ለአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን ለትውልድ ሁሉ የሚተርፍ የታሪክ ዐሻራ ማሳያ መሆናቸውንም አስታውቀዋል። በተያያያዘም፤ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ በዘመናዊው ታሪክ ውስጥ እጅግ ፈታኝ በሆነ ወቅት ላይ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር ጥልቅ አድናቆታችንን እንገልጻለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የተባበሩት መንግሥታት የጸናው ሀገራት ከመከፋፈል ይልቅ ውይይትን ስለመረጡ መሆኑን አስገንዝበው፤ ኢትዮጵያም ይህንኑ የሁልጊዜ ምርጫዋን ታጸናለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም የምክክር ባህል እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበው፤ ጠንካራ የሲቪክ ማኅበረሰብ ባህል ግንባታ ደግሞ ያላሰለሰ የመነጋገር ልምምድ እና የሰከነ የወል መደማመጥን ግድ ይላል ብለዋል። የእስካሁን ሂደቱም በማኅበረሰባችን በየደረጃው የመደማመጥን ከፍ ያለ ጠቀሜታ አሳይቷል ሲሉም ገልጸዋል። ሂደቱ በሀገራችን ሁሉም ማዕዘናት የሚገኙ ከ90 በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን አመለካከቶች እና የውይይት ውጤቶች ያንፀባረቀ ሆኗልም ነው ያሉት። ለሀገር ወሳኝ ፋይዳ የያዘው የምክክሩ ምዕራፍ ተጨባጭ ውጤት ወደሚያስገኘው ቀጣይ ምዕራፍ በሚሸጋገርበት በዚህ ወቅት፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለሀገራችን ሰላም፣ አንድነት እና ዘላቂ መረጋጋትን የሚያረጋግጥ የጋራ ፅኑ አቋም እና ገንቢ በሆነ መንገድ አስተዋፅኦ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል። · የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን በመረቁበት ወቅት፤ ፓርኩ አስተማማኝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጀመርነው የብልጽግና ጉዞ ተደማሪ እመርታ ነው ብለዋል። ለመካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች ምቹ የንግድ ከባቢ ከመፍጠር ባሻገር በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶቻችን የሥራ ዕድል ይከፍታል ሲሉም ገልፀዋል። ፓርኩ የሀገራችን አምራቾች አቅማቸውን በማጎልበት፣ ምርታማነታቸውን ማሳደግና ተወዳዳሪነታቸውን በመጨመር ለከተማችን፣ ለሀገራችንና ለቀጣናው የሚተርፉበት ታላቅ እድልን ይዟል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተኪ ምርቶችን በማምረት በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛና ቀልጣፋ የንግድ ትስስር ይፈጥራል፤ ምርቶችን ደግሞ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይጫወታል ሲሉ አስረድተዋል። · ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ መጀመር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔን ባስጀመሩበት ወቅት፤ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ቆራጥ ጥረት ውስጥ የሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል በማድረግ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በመላ ሀገሪቱ ከ35 ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት የነጻና አስገዳጅ ትምህርት ተደራሽ እንዲሆን እያደረግን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር ላይ መሥራት በመሆኑ ተባብረን፣ በጊዜ የለንም መንፈስና በትጋት እንሥራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። · የፖሊሲ ቀን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ ባሳላፍነው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው የፖሊሲ ቀን ተከብሯል። በዚሁ ወቅትም፤ ውጤታማ ፖሊሲ ለሀገራዊ ዕድገት የጀርባ አጥንት መሆኑን አስገንዝበው፤ መንግሥት በግልፅ፣ ተተግባሪና ጥራት ባላቸው ፖሊሲዎቹ ለሕዝብ የገባውን ቃል እየተገበረ ስኬትም እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ሀገራችን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ በጂኦ-ፖለቲካዊና በቴክኖሎጂ ለውጦች ላይ ቀድሞ ምላሽ የሚሰጡ ጥናቶች ያስፈልጋሉ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በዕውቀት ላይ ኢንቨስት በማድረግ እና ለማስረጃዎች ዋጋ በመስጠት፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ የፖሊሲ ሥነ-ምኅዳር ለመገንባት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ለዚህ ስኬት ሁላችንም በጋራ እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
የጤና ነገር
May 15, 2026 1138
በዮሐንስ ደርበው ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ሾተላይ የሚከሰተው RH-Negative የሆነች እናት RH-Positive የሆነ ፅንስ በምታረግዝበት ወቅት የእናትየው በሽታ የመከላከል ሥርዓት የፅንሱን ደም እንደ ባዕድ ነገር በመቁጠር በሚያመነጨው ንጥረ-ነገር (Antibodies) አማካኝነት መሆኑን የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። የጽንስና ማህጸን ስፔሻሊስት ዶክተር ዳንኤል ኃብተማርያም ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ከወሊድ ጋር በተያያዘው አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ወይም ሾተላይ እየተባለ በሚጠራው በጽንስ ላይ የሚያጋጥም ችግር ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሾተላይ ወይም አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ዳንኤል ማብራሪያ፤ ሰዎች ከሚታወቁበት አራቱ የደም ዓይነቶች ምደባ (ኤ፣ ቢ፣ ኤቢ እና ኦ) በተጨማሪ በቀይ ደም ኅዋስ ሰርፌስ ላይ በፕሮቲን መኖርና አለመኖር ይለያሉ። በዚህም መሠረት አር ኤች ፖዘቲቭ (RH+) እና አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ተብለው እንደሚከፈሉ ያስረዳሉ። በዚህ ምደባ መሠረት ከአጠቃላይ ሕዝቡ 85 በመቶው አር ኤች ፋክተር ፖዘቲቭ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ማለት በቀይ ደም ኅዋሳቸው ሰርፌስ ላይ ፕሮቲን አላቸው ማለት ነው ይላሉ። 15 በመቶው ደግሞ አር ኤች ኔጌቲቭ ወይም በቀይ የደም ኅዋሳቸው ሰርፌስ ላይ ፕሮቲን የሌላቸው ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። አክለውም አር ኤች ኔጌቲቭ ወይም ፖዘቲቭ መሆን በሽታ እንዳልሆነ በአጽንኦት ገልጸው፤ ከወላጆች የሚወረስ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ አንድ ልጅ ሲወለድ እንደ ወላጆቹ አር ኤች ፋክተር መሠረት አር ኤች ፖዘቲቭ ወይም አር ኤች ኔጌቲቭ ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። ይህን በምሳሌ ሲያስረዱም፤ አንዲት ሴት አር ኤች ፋክተሯ ኔጌቲቭ ሆኖ ጽንሷ ደግሞ አር ኤች ፖዘቲቭ ቢሆን ተገቢው የሕክምና ክትትል ካልተደረገ ብሎም የእናትና ልጅ ደም ንክኪ ከተፈጠረ የበሽታ መከላከል ሥርዓቷ የሚያመነጨው አንቲ ቦዲ ጽንሱን እንደ ባዕድ ነገር ስለሚቆጥረው ጉዳት (ሾተላይ) ያስከትላል ይላሉ። የአንቲ ቦዲ ሥራ ሴቷ ለአር ኤች ፖዘቲቭ የምትጋለጥበት ሁኔታ ከተፈጠረ ጽንሱን (አር ኤች ፋክተሩ ከእሷ ተቃራኒ ሲሆን) እንደ ባዕድ ነገር ቆጥሮ ሴትዮዋን ለመከላከል በጽንሱ ላይ ጥቃት ማድረስ መሆኑንም አመላክተዋል። መፍትሔው ምንድን ነው? ለማንኛውም ጤናማ የእርግዝና ሂደት የሕክምና ክትትል ማድረግ ቀዳሚ መፍትሔ መሆኑን መክረዋል። ከሾተላይ ጋር በተያያዘ ደግሞ በእርግዝና ወቅት የሚስትና ባልን አር ኤች ፋክተር መለየት ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህን ተከትሎም አር ኤች ፋክተራቸው ተመሳሳይ ከሆነ ጽንሱም ከእነሱ ጋር ስለሚመሳሰል ጤናማ እንደሚሆን ገልጸዋል። በአንጻሩ ግን፤ አር ኤች ፋክተሯ ኔጌቲቭ የሆነች ሴት የባለቤቷ አር ኤች ፋክተር ፖዘቲቭ ከሆነ ወይም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ ሰውነቷ መከላከያ አምርቷል ወይስ አላመረተም የሚለው በሕክምና ምርመራ እንደሚታወቅ አስረድተዋል። ይህ ምርመራ ሲሠራ ውጤቱ ኔጌቲቭ ከሆነ ወይም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ ሰውነቷ መከላከያ አላመረተም የሚል ከሆነ በዚህኛው እርግዝናም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ፣ የእናትና የጽንስ ደም ንክኪ ኖሮ መከላከያ እንዳታመርት የሚሰጥ ሕክምና እንዳለ አረጋግጠዋል። ይህ ሕክምናም 28ኛ ሳምንት ላይ በመርፌ ለመጀመሪያ ጊዜ ይሰጣል ብለዋል። ከወለደች በኋላ ደግሞ የተወለደው ልጅ አር ኤች ፋክተር ታይቶ እንደእናቱ ከሆነ ተጨማሪ መድኃኒት እንደማያስፈልግና ከአባቱ ጋር ከተመሳሰለ ግን (አር ኤች ፖዘቲቭ ከሆነ) በመርፌ ተጨማሪ መድኃኒት በወለደች በ72 ሠዓት ውስጥ በመስጠት ለቀጣይ እርግዝናዎች ሰውነቷ መከላከያ እንዳያመነጭ ማድረግ እንደሚቻል አብራርተዋል። በሌላ በኩል ከሾተላይ ጋር በተያያዘ የሚደረጉ ሳይንሳዊ ያልሆኑ ልማዳዊ ድርጊቶችን ኮንነው፤ ትክክለኛው መፍትሔ ያለው የሕክምና ክትትል በማድረግ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲሁም፤ በተለይም የጎንዮሽ ህመም ያለባቸው ሴቶች (የኩላሊት፣ የደም ግፊት፣ ስኳር እና ሌሎችም) ቀድመው ሐኪም አማክረው ወደ እርግዝና ቢገቡ እንደሚመከር ገልጸው፤ የቅድመ እርግዝና ክትትል ማድረግ ካልተቻለ እንኳን በእርግዝና ወቅት በአግባቡ ክትትል ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል። ለመከላከያ ትልቅ ትኩረት መስጠት ችግሩ ተፈጥሮ ከመታከም የተሻለና ተመራጭ መፍትሔ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። #የጤና_ነገር #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት
ለተቃና ነገ የኢትዮጵያ ትጋት አንዱ መገለጫ
May 11, 2026 1794
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ ከምትከውናቸው ዐበይት ጉዳዮች መካከል ሰው ተኮር ተግባራት ቀዳሚው ነው። በአዲስ አበባ በተካሄደው ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ጥረት ሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ ነው ብለዋል። መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል አድርጎ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በዚህም መሠረት፤ የልጆች ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት፣ የምገባ ሥርዓትን ማሳደግ፣ የሕጻናት መጫወቻ ሥፍራዎች ግንባታ ላይ ተጨባጭ ውጤቶች መምጣታቸውንም ነበር የጠቀሱት። ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማትና ትምህርት ፖሊሲ የዘላቂ ብልጽግና መንገዳችን ከሆነው የመደመር ዕሳቤ ጋር በተናበበ መልኩ እየተተገበረ በስኬት ቀጥሏልም ብለዋል። ኢትዮጵያ ለነገ የተዘጋጀ ትውልድ ለመገንባት በሕግና በፖሊሲ የተደገፉ የቀዳማይ ልጅነት ኢኒሼቲቮችን እየተገበረች እንደምትገኝም አስታውቀዋል። ለአብነትም፤ በ2015 ተሻሽሎ የፀደቀው ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማት እና ትምህርት የፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲሁም በ2017 የፀደቀውን አጠቃላይ የትምህርት አዋጅ መሠረት በማድረግ ከ35ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላው ሀገሪቱ እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል። በመንግሥት ተቋማት የሕጻናት ማቆያ ማዕከላት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በመጠቆምም፤ ኢትዮጵያ የሕጻናትን ደኅንነት ማሻሻል የሚያስችል ጉልኅ ብሔራዊ መርሐ-ግብር መጀመሯን አንስተዋል። በሰቆጣ ቃል ኪዳን አማካኝነት የ15 ዓመት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ ከሁለት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ላይ የሚደርሰውን መቀንጨር በ2022ዓ.ም ዜሮ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። የሌማት ትሩፋትና የአልሚ ምግቦች ምርታማነት የሕጻናትን ጉዳት ለመቀነስና የልጆችን ጤናማነት መጨመር እያስቻሉ እንደሚገኙም ነው የተናገሩት። ኢትዮጵያ ለዘላቂ የልማት ግቦችና ለሕጻናት መብቶች ጥበቃ የገባቻቸውን ቃል ኪዳኖች ወደ ተግባር እየለወጠች መሆኑን በማንሳት፤ ይህንንም አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። መንግሥት ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን በመላ ሀገሪቱ ለማስፋት ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑንም አመላክተዋል። በዚህም መሠረት፤ በጀት በመመደብ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል፣ የተማሪዎችን ምገባ በማስፋፋት ውጤት ማምጣቱን ነው የሚያብራሩት። ልጆች በአካልና በመንፈስ የሚጎለብቱባቸው የስፖርትና የመዝናኛ ቦታዎች በየአካባቢው በመገንባት፣ በኮሪደር ልማት ለልጆች ምቹ ሥፍራ እየተፈጠረ መሆኑንም በመጥቀስ። ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር፣ አኅጉር እና ዓለም ላይ መሥራት በመሆኑ በትጋት ማስቀጠል እንደሚገባም በአጽንኦት ይናገራሉ። አፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ተግዳሮቶችን ለመፍታት የራሷን መፍትሔዎች በማፍለቅ፣ በብሔራዊ የልማት አጀንዳዋ እያካተተች መሆኑን የሚገልጹት ደግሞ የአፍሪካ ቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ከበደ ወርቁ ናቸው። በሕጻናት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ማንኛውም ሀገር በመጪው ትውልድ ላይ ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው እጅግ አስፈላጊ ኢንቨስትመንቶች አንዱ መሆኑንም ያነሳሉ። አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ ያሉባትን ተግዳሮቶች ከመጋፈጥ ባለፈ፤ የራሷን መፍትሔዎች እያመነጨች መሆኑንና ጉዳዩን የብሔራዊ ልማት አጀንዳዋ አካል እያደረገችው እንደምትገኝም ገልጸዋል። አዲስ አበባ ይህን ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ እንድታስተናግድ የተመረጠችበት ዋና ምክንያትም፤ በዘርፉ እያከናወነች ያለው ተግባር አርዓያነት ያለው በመሆኑ ነው ብለዋል። ከተማዋ የጤና እና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎቶችን ያካተተ የተቀናጀ ዘርፈ-ብዙ አሠራር መዘርጋቷን ጠቅሰው፤ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት እና የቀን የሕጻናት እንክብካቤ ማዕከላትን በከተማ አቀፍ ስትራቴጂ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝም ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው፤ መዲናዋ በቀዳማይ ልጅነት ያመጣችው ተጨባጭ ውጤት በአርዓያነት እንድትጠቀስ እንዳደረጋት አንስተዋል። በሕጻናት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች፤ በትምህርት፣ በሰው ሃብት ልማትና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ፋይዳ እንዳለውም አስረድተዋል። በዚህም በአዲስ አበባ ፍትሐዊና አካታች የቀዳማይ ልጅነት ልማት መርሐ-ግብርን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ የትውልድ ግንባታ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል። "ሕጻናት የአዲስ አበባ የነገ ተስፋዎች" የሚል ፍኖተ ካርታ በመቅረጽ 1 ነጥብ 3 ሚሊየን ለሚሆኑ ከስድስት ዓመት በታች ሕጻናት ሁለንተናዊ ዕድገት መረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በትምህርት ቤት ምገባ መርሐ-ግብርም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ ዩኒፎርምና በቀን ሁለት ጊዜ ምግብ በማቅረብ በሕጻናት ክብካቤ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል ነው ያሉት። የሕጻናት ማቆያና መጫወቻ የመሠረተ-ልማት ግንባታ፤ ሕጻናት ነፃ የሕክምና፣ የምገባና የሥነ-ልቦና አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። የቀዳማይ ልጅነት መርሐ-ግብር በ2015 ዓ.ም ሲጀመር በዕድገት ወደ ኋላ የቀሩ የሕጻናት መጠን ከነበሩበት 13 በመቶ አሁን ላይ ወደ 10 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉን ከንቲባዋ አመላክተዋል። አክለውም፤ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዝግጁነታቸው ከነበረበት 49 በመቶ አሁን ወደ 90 በመቶ ማደጉንም ተናግረዋል። ሀገር በሁሉም ዘርፍ የበቃ መጪ ትውልድ እንዲኖራት መንግስት የያዘው ጥረት በሚፈለገው መጠን ለውጤት እንዲበቃ የሁሉንም ትኩረትና ተሳትፎ ይሻል። ለነገ በሁሉም ዘርፍ የዳበረ ትውልድና የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን ዛሬ ላይ እየተደረገ ያለው ርብርብ የሀገራችንን መፃኢ ብሩህ ተስፋ ይበልጥ የሚያለመልም ነውና ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 5892
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 3705
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 9498
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 7979
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 718
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 1857
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።