ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የመደመር ፍሬ፡አረንጓዴዋ ኢትዮጵያ
Aug 5, 2026 164
በሙሴ መለሰ የመደመር እሳቤ ዋና መሠረቱ እውቀትን፣ጉልበትን፣ሀብትንና አቅምን አስተባብሮ ለአንድ የጋራ ዓላማ በጋራ ማቆምን ያመለክታል። ይህን የሃሳብ ልዕልና በተግባር ፈትሾ ተጨባጭ ውጤት የታየበት ላለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ነው። አረንጓዴ ዐሻራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን አግኝቷል። የአረንጓዴ ዐሻራ ትልቁ ማሳያ የህዝብ ህብረት የታየበት መሆኑ ነው። በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እድሜ፣ ጾታ እና ልዩነት ሳይበግራቸው በነቂስ በመውጣት በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል አኩሪ ታሪክ የሰሩበት ህዝባዊ ንቅናቄ የመደመርን አስተሳሰብ በተግባር ያረጋገጠ ነው። ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ ከተካሄደው የአንድ ጀምበር መርሃ ግብር እንደታየው፣መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያለ ምንም ክፍያ በሙሉ ፈቃደኝነት እና በዝናብ ውስጥ ውሎ ከ805 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ሰርቷል። በአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላው 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ተደምረው ለነገ ልጆቻቸው መሰረት ለመጣል ሲወስኑ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ለዓለም ህዝብ ያሳዩበት ህያው አብነት ነው። የመደመር እሳቤ በቃላት ሳይሆን በተጨባጭ ውጤት የሚለካ ነው፤ በዘንድሮው የችግኝ ተከላ ዘመቻ እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ቀሪው 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ደግሞ በቀጣይ ጊዜያት ይተከላል። በአንድ ወቅት ከ40 በመቶ በላይ የደን ሽፋን የነበራት ኢትዮጵያ ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሃብትና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት የደን ሽፋኗ ወደ 3 በመቶ ወርዶ ነበር። አረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ የደን ሽፋን ከነበረበት 17.2 ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በማሳደግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ችግኝ ተከላው ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ከምግብ ዋስትና እና ከሀገር ኢኮኖሚ ጋርም የተሳሰረ ነው። በፍራፍሬ እንደ አቮካዶ፣ማንጎ እና ቡና ባሉ ምርታማ ችግኞች ላይ በማተኮሩ የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባሻገር፣ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት የምትበለጽግ፣የማትለምን እና ለተቸገሩት የምትደርስ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል የዜጎችን ገቢ የማሳደግ ድርሻ አለው። ኢትዮጵያ ችግኞችን ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ያከናወነቻቸው የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስራዎች የመደመር እሳቤ ድንበር አቋርጦ ለአህጉራዊ ትስስር እና ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ የሚሆን ድንበር ተሻጋሪ እሴት እንዳለው ያሳያል። ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዋ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ ምክንያት ሆኗል። ይህም የኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት ዓለም አቀፍ እውቅናን አስገኝቷል። በአጠቃላይ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያን በቀና እሳቤ እና በትብብር በመቆም ተስፋን ለልጆቻቸው መዝራት እንደሚችሉ በተግባር፣በስራና በውጤት ያረጋገጡበት ትልቅ ሀገራዊ ኩራት ነው።
በሆስፒታሉ የኦክስጅን ማምረቻ ማዕከልን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎት መስጫዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረጉ
Aug 5, 2026 137
ባህርዳር ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ በባህር ዳር ከተማ ፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተገነባ የኦክስጅን ማምረቻ ማዕከልን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎት መስጫዎች የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረጉ። በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱን ጨምሮ ሌሎች የዘርፉ የስራ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን የሆስፒታሉ የስራ እንቅስቃሴም ተጎብኝቷል ። በሆስፒታሉ ከኦክስጅን ማምረቻ ማዕከል በተጨማሪ የጨቅላ ህፃናት ህክምና ማዕከልና የዲጂታል ቋት ምረቃ የተካሄደ ሲሆን የተለያዩ አገልግሎቶችና የቀዶ ህክምና ክፍል የእድሳት ማስጀመሪያ ስነ ስርአት ተከናውኗል።   በሆስፒታሉ የኦክስጅን ማምረቻ ማዕከል መገንባት የህክምና አገልግሎት አሰጣጡን የተሟላ እንደሚያደርገው የሆስፒታሉ የባዮ ሜዲካል ክፍል አስተባባሪ ውዴ በቀለ ለኢዜአ ገልፀዋል። ማእከሉ በአመት 28ሺህ 800 ሲሊንደር ኦክሲጅን የማምረት አቅም እንዳለው ጠቁመው ይህም ምርቱን ከሆስፒታሉ ባለፈ ለሌሎች በአካባቢው ለሚገኙ ጤና ተቋማት የማቅረብ አቅም እንደሚኖረው አመላክተዋል ። በስነ ስርአቱ የችግኝ ተከላ ተካሂዷል። በነገው እለትም ሚኒስትሯ በተገኙበት በጤናው ዘርፍ የሚመክር መድረክ በባህር ዳር ከተማ እንደሚካሄድ ተመላክቷል።
የምክክር ጉባዔው ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ዕድል የፈጠረ ነው
Aug 5, 2026 198
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ዕድል የፈጠረ መሆኑን የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛል። በብሪታንያ እና በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባቶች እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር የጋራና አካታች በመሆኑ ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው።   በብሪታኒያ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባት ኡስታዝ ሙክታር ጀማል እንዳሉት በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር ኢትዮጵያ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ያስፈልጋት የነበረ ታላቅ እርምጃ ነው። ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ሂደት ነው ብለዋል። በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባት ፓስተር አረጋ ሽፈራሁ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አካታችና አሳታፊ መሆኑንና እያንዳንዱ ተመካካሪ ሃሳቡን ያንፀባረቀበት ሁሉም በኢትዮጵያ ልማት፣ ሰላምና ልማት እየመከረ ይገኛል ብለዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ማስረከብ የሚያስችል ነው
Aug 5, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ የሚያስችል ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ስምንት የምክክር አጀንዳዎችን በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የምክክር ጉባዔ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው ምክክር አራት ሺህ ተመካካሪዎች እየመከሩ ይገኛሉ። በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ ያሉ ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ያስችላል። የምክክር ሂደቱ ሁሉም ዜጋ ለሀገሩ የድርሻውን የሚያበረክትበት ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን በመግለጽ፣ ለሀገር ግንባታ የሚረዱ ሀሳቦችን እያንሸራሸሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ተመካካሪ ከተማ ባህሩ እንደገለጹት፣ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው በአጀንዳዎች ዙሪያ ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ጠንካራ መድረክ ሆኖ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ መድረኩ የሀሳብ ብዝሃነትን በአግባቡ የሚያስተናግድና ሁሉም ተመካካሪዎች ሃሳባቸውን በነጻነት እንዲያንሸራሽሩ ሰፊ ዕድል ያመቻቸ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በመሆኑም ሂደቱ ሁሉንም የህብረተሰቡን ክፍሎች ያሳተፈና አካታች በመሆኑ ለሀገራዊ አንድነትና ውይይት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ተመካካሪ እቴነሽ ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አካታች መሆኑን በመግለጽ፣ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ትልቅ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክክሩ አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን በመጠቆም፣ ሁሉንም ያሳተፈ መሆኑንና በሁሉም ጉዳዮች ላይ በግልጽ እየተወያዩ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ እያካሄድነው ያለው ሀገራዊ ምክክር ለመጭው ትውልድ ደህንነቷ የተጠበቀ እና ሰላሟ የተረጋገጠች ሀገር ለማስረከብ የሚያስችል ነው ያለው ተመካካሪ ደግሞ አብዱላዚዝ አብዲ ነው፡፡ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባት የተፈጠረባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ተስፋ እንዳለውም ተናግሯል።
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 165
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
የሚታይ
የመደመር ፍሬ፡አረንጓዴዋ ኢትዮጵያ
Aug 5, 2026 164
በሙሴ መለሰ የመደመር እሳቤ ዋና መሠረቱ እውቀትን፣ጉልበትን፣ሀብትንና አቅምን አስተባብሮ ለአንድ የጋራ ዓላማ በጋራ ማቆምን ያመለክታል። ይህን የሃሳብ ልዕልና በተግባር ፈትሾ ተጨባጭ ውጤት የታየበት ላለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ነው። አረንጓዴ ዐሻራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን አግኝቷል። የአረንጓዴ ዐሻራ ትልቁ ማሳያ የህዝብ ህብረት የታየበት መሆኑ ነው። በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እድሜ፣ ጾታ እና ልዩነት ሳይበግራቸው በነቂስ በመውጣት በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል አኩሪ ታሪክ የሰሩበት ህዝባዊ ንቅናቄ የመደመርን አስተሳሰብ በተግባር ያረጋገጠ ነው። ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ ከተካሄደው የአንድ ጀምበር መርሃ ግብር እንደታየው፣መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያለ ምንም ክፍያ በሙሉ ፈቃደኝነት እና በዝናብ ውስጥ ውሎ ከ805 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ሰርቷል። በአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላው 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ተደምረው ለነገ ልጆቻቸው መሰረት ለመጣል ሲወስኑ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ለዓለም ህዝብ ያሳዩበት ህያው አብነት ነው። የመደመር እሳቤ በቃላት ሳይሆን በተጨባጭ ውጤት የሚለካ ነው፤ በዘንድሮው የችግኝ ተከላ ዘመቻ እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ቀሪው 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ደግሞ በቀጣይ ጊዜያት ይተከላል። በአንድ ወቅት ከ40 በመቶ በላይ የደን ሽፋን የነበራት ኢትዮጵያ ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሃብትና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት የደን ሽፋኗ ወደ 3 በመቶ ወርዶ ነበር። አረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ የደን ሽፋን ከነበረበት 17.2 ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በማሳደግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ችግኝ ተከላው ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ከምግብ ዋስትና እና ከሀገር ኢኮኖሚ ጋርም የተሳሰረ ነው። በፍራፍሬ እንደ አቮካዶ፣ማንጎ እና ቡና ባሉ ምርታማ ችግኞች ላይ በማተኮሩ የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባሻገር፣ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት የምትበለጽግ፣የማትለምን እና ለተቸገሩት የምትደርስ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል የዜጎችን ገቢ የማሳደግ ድርሻ አለው። ኢትዮጵያ ችግኞችን ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ያከናወነቻቸው የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስራዎች የመደመር እሳቤ ድንበር አቋርጦ ለአህጉራዊ ትስስር እና ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ የሚሆን ድንበር ተሻጋሪ እሴት እንዳለው ያሳያል። ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዋ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ ምክንያት ሆኗል። ይህም የኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት ዓለም አቀፍ እውቅናን አስገኝቷል። በአጠቃላይ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያን በቀና እሳቤ እና በትብብር በመቆም ተስፋን ለልጆቻቸው መዝራት እንደሚችሉ በተግባር፣በስራና በውጤት ያረጋገጡበት ትልቅ ሀገራዊ ኩራት ነው።
የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በኦንላይን ክፍያ መፈጸም ይጠበቅባቸዋል
Aug 5, 2026 261
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ መልዕክት የደረሳቸው የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በኦንላይን ክፍያቸውን በመፈጸም የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቀረበ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰውነት አየለ በሰጡት መግለጫ፣ቢሮው የግብር ስርዓቱን በማዘመን እና ፍትሃዊ አሰባሰብን በመዘርጋት ገቢን በጥራት እየሰበሰበ ይገኛል ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ ከሚሰበስበው ገቢ 72 በመቶውን ለዘላቂ ልማት፣ ለሰው ተኮር ፕሮጀክቶች እና ለኮሪደር ልማት በማዋል የመዲናዋን ገጽታና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እያጎለበተ ይገኛልም ብለዋል። በከተማዋ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ ከ456 ሺህ በላይ የደረጃ «ለ» ግብር ከፋዮች አዲስ በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ መሰረት ግዴታቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ከደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች በዘንድሮ በጀት ዓመት 9.2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል። መረጃቸው ለተሟላላቸው ግብር ከፋዮች የግብር ውሳኔ በስልክ የጽሁፍ መልዕክት የተላከ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ ግብራቸውን በወቅቱ መክፈላቸውን አንስተዋል። እስከ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም መልዕክት የደረሳቸው ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በኦንላይን በመክፈል ከቅጣት እና ወለድ ራሳቸውን መጠበቅ ይኖርባቸዋል ብለዋል። በተለያዩ ምክንያቶች መልዕክት ያልደረሳቸው ወይም ከሐምሌ 25 በኋላ የደረሳቸው ግብር ከፋዮች መልዕክቱ ከተላከላቸው ጊዜ ጀምሮ እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ ያለ ቅጣት ግብራቸውን መክፈል እንደሚችሉ አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት ያሳያል 
Aug 5, 2026 207
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን የቤኒን የዲጂታል ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን ገለጹ፡፡ በቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የተመራ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ የአምስት ቀን የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ መግባቱ ይታወቃል።   በዚህም መሰረት ሚኒስትሩና የልዑካን ቡድናቸው በኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትና በፋይዳ ቨርስ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ፈጣን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግር እየተደረገ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን በአጭር ጊዜ አስገራሚ የዲጂታል መሰረተ ልማት በመገንባትና ፈጣን የመንግሥት አገልግሎት ስርዓት ላስመዘገቡት ዕምርታ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያና ቤኒን መካከል ያለው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክፍተት በጋራ መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ልምድ መለዋወጥ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት በግልጽ እንደሚያሳይ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በዲጂታል መሰረተ ልማት እያደገች መሆኑን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ከዚህ መማር አጀንዳችንን ለማቀላጠፍ ያግዘናል ብለዋል፡፡ ቤኒን በሳይበር ደህንነት ያላትን ጠንካራ አቅም ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለማሳደግ በአቅም ግንባታና በዕውቀት ልውውጥ በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡ የፋይዳ ቨርስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮዳሔ አርዓያሥላሴ በበኩላቸው፤ የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ለኢትዮጵያ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል፡፡   የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ለዲጂታል ዲፕሎማሲ አቅም ግንባታ የጎላ አበርክቶ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ብዙ የተለመደው ከአውሮፓ ወይም ከኤዥያ የሚመጣን ስርዓት ማስተዳደር ነው ያሉት አቶ ዮዳሔ፤ ቴክኖሎጂን በራስ አቅም መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ሁሉም መገንዘቡን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የራሷን ቴክኖሎጂዎች በማፍለቅ ለሌሎች ትምህርት መስጠቷ አፍሪካውያን በራሳቸው እንዲተማመኑና ዕምነት እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ስያሜውንና ተልዕኮውን በመቀየር ራሱን ችሎ የመንግሥት የልማት ድርጅት ሆኖ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥር መካተቱን አንስተዋል፡፡ ይሄውም አገልግሎቱን ከኢትዮጵያ ውጪ በማስፋት በአፍሪካ ሀገራት ጭምር የማማከርና ስርዓት የመገንባት ዕድሎችን የምናገኝበት ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ የኢፌዴሪ የመሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ አለማየሁ፤ መሶብ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን አሻሽሏል ብለዋል፡፡   በኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ 108 የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በመክፈት ከ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ማገልገል ተችሏል ብለዋል፡፡ ከ220 በላይ አገልግሎቶችን በላቀ ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊ አሰራር በመስጠት የተገልጋዮችን እርካታ 98 በመቶ ማድረስ እንደተቻለም ገልጸዋል፡፡ መሶብ የኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የመሻገር ህልም መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ ሀገራት ልምድ የሚወስዱበትና የዲፕሎማሲ ተግባቦት የሚፈጠርበት ነው ብለዋል፡፡ የቤኒን ብቻ ሳይሆን የሌሎች ዓለም ሀገራት ጭምር አይተው የሚደነቁበት መሆኑን በማንሳት ጉብኝቱ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ብዙ ርቀት መጓዟን እንደሚያሳይ ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን ኢንጂነሮችና በኢትዮጵያ ሀብት የለማ መሆኑ ኢትዮጵያውያን እውቀትና አቅማችንን አስተባብረን መስራት እንደምንችል አሳይቷል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ንጹሕና አረንጓዴ ከተሞችን በመገንባት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተምሳሌት እየሆነች ነው
Aug 5, 2026 216
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ኢትዮጵያ ከተሞቿን አረንጓዴ፣ ንጹሕና ዘመናዊ የኑሮ ማዕከላት በማድረግ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ኦፊሰር ኸርነስት ቺ ቾ ገለጹ። ኦፊሰሩ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በአዲስ አበባ የአረንጓዴ ከተማ ፖሊሲዎች በተግባር መተግበራቸውና ሰፊ የመሠረተ ልማት ሥራዎች መከናወናቸው በከተማዋ ሁለንተናዊ ለውጥ እንዲመዘገብ አስችሏል። በተለይም በአዲስ አበባ ጎዳናዎች፣ ፓርኮችና የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች ላይ የታዩ ተጨባጭ ለውጦች ከተማዋን የተሻለ የኑሮ አካባቢ እንዲሆን እያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።   ከ10 ዓመታት በፊት ወደ አዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ መምጣታቸውን ያስታወሱት ኦፊሰሩ፣ የመንገድና የከተማ መሠረተ ልማቶች አሁን ከቀድሞው ጋር ሲነጻጸሩ እጅግ አስደናቂ ለውጥ እንዳሳዩ ገልጸዋል። ዘመናዊ ከተማ ማለት የተሻለ ደህንነት ያላቸው መንገዶች፣ አረንጓዴ የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎችና የተሟሉ መሠረተ ልማቶች ያሉባት ከተማ ናት ነው ብለዋል። በዚህም በአዲስ አበባ የፓርኮች፣ የሕፃናት መዝናኛ ስፍራዎችና ሌሎች የሕዝብ መገልገያዎች በስፋት መገንባታቸው የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት ስኬትም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያግዙ፣ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የማስፋፋት ጥረቶችም ወሳኝ የለውጥ አካል መሆናቸውን አክለዋል። ኢትዮጵያ ከተሞቿን አረንጓዴና ንጹሕ በማድረግ ለሌሎች ሀገራት አርዓያ መሆኗን ቀጥላለች ብለዋል።   በቱሪዝም ዘርፍም ኢትዮጵያ ተጨባጭ ለውጦችን በማስመዝገብ በአፍሪካ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑና ጥራታቸውን የጠበቁ በርካታ ሆቴሎች መገንባታቸው የዘርፉን ዕድገት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የተከናወኑ የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ሥራዎች ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አርዓያ ናቸው ያሉት ኦፊሰሩ፣ የኢትዮጵያ የሆቴሎች ጥራትና ብዛት በብዙ የአፍሪካ ከተሞች ከሚታየው እንደሚልቅ ገልጸዋል።   በሌላ በኩል የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ማግኘቱን ጠቅሰው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአፍሪካ ሞዴል የሆነ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።
የምክክር ጉባኤው በተቀመጠለት መርሀ-ግብር መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል
Aug 5, 2026 201
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018(ኢዜአ)፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተቀመጠለት መርሀ-ግብር መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እየተካሄደ የሚገኘውን የምክክር ጉባኤ አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም ምክክሩ አሁን ላይ በስልታዊ ቡድኖች ደረጃ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተመካካሪዎች ከ10 እና ከ50 አነስተኛ ቡድኖች ተነስተው 250 አባላት ባሏቸው ስልታዊ ቡድኖች ውስጥ የደረሱባቸውን ሀሳቦች አጠናቅረው በማቅረብ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በየደረጃው ያሉ ምክክሮች በቃለ-ጉባኤ ተይዘውና ተፈራርመው ወደ ሚቀጥለው ደረጃ እንደሚሸጋገሩ ያመላከቱት ዋና ኮሚሽነሩ፣ የስልታዊ ቡድኑ ስራ ሲጠናቀቅ ተሳታፊዎቹ ወደ 500 አባላት ዋና ጉባኤ እንደሚሸጋገሩ ገልጸዋል፡፡ ለተመካካሪዎቹም 160 ገደማ አመካካሪዎች እና የተለያዩ የሙያ ዘርፍ ባለሙያዎች እውቀትን መሠረት ያደረገ የተለያዩ ገለጻዎችን እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡ በምክክሩ ላይ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮች፣ ምሁራን፣ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች በእኩል ደረጃ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሁሉም አካላት የሀገርን የጋራ ጥቅም ማዕከል በማድረግ እና የእርስ በእርስ እኩልነትን ባከበረ መልኩ ለምክክሩ ውጤታማነት በጋራ እየመከሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ቃለ-ጉባኤ ያዦቹ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች መሆናቸውንና እያንዳንዷን ነጥብ ለወደፊት ተመራማሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች በሚጠቅም መልኩ በታማኝነት እየሰነዱ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል፡፡ የምክክሩ ሂደቱ በተቀመጠለት መርሃ ግብር መሰረት በጥሩ ሁኔታ እየካሄደ መሆኑንና ሁሉም ወገኖች ሀገራዊ መግባባት ላይ ለመድረስ እየመከሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የምክክር ጉባዔው ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ዕድል የፈጠረ ነው
Aug 5, 2026 198
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ዕድል የፈጠረ መሆኑን የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛል። በብሪታንያ እና በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባቶች እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር የጋራና አካታች በመሆኑ ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው።   በብሪታኒያ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባት ኡስታዝ ሙክታር ጀማል እንዳሉት በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር ኢትዮጵያ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ያስፈልጋት የነበረ ታላቅ እርምጃ ነው። ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ሂደት ነው ብለዋል። በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባት ፓስተር አረጋ ሽፈራሁ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አካታችና አሳታፊ መሆኑንና እያንዳንዱ ተመካካሪ ሃሳቡን ያንፀባረቀበት ሁሉም በኢትዮጵያ ልማት፣ ሰላምና ልማት እየመከረ ይገኛል ብለዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ማስረከብ የሚያስችል ነው
Aug 5, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ የሚያስችል ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ስምንት የምክክር አጀንዳዎችን በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የምክክር ጉባዔ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው ምክክር አራት ሺህ ተመካካሪዎች እየመከሩ ይገኛሉ። በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ ያሉ ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ያስችላል። የምክክር ሂደቱ ሁሉም ዜጋ ለሀገሩ የድርሻውን የሚያበረክትበት ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን በመግለጽ፣ ለሀገር ግንባታ የሚረዱ ሀሳቦችን እያንሸራሸሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ተመካካሪ ከተማ ባህሩ እንደገለጹት፣ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው በአጀንዳዎች ዙሪያ ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ጠንካራ መድረክ ሆኖ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ መድረኩ የሀሳብ ብዝሃነትን በአግባቡ የሚያስተናግድና ሁሉም ተመካካሪዎች ሃሳባቸውን በነጻነት እንዲያንሸራሽሩ ሰፊ ዕድል ያመቻቸ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በመሆኑም ሂደቱ ሁሉንም የህብረተሰቡን ክፍሎች ያሳተፈና አካታች በመሆኑ ለሀገራዊ አንድነትና ውይይት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ተመካካሪ እቴነሽ ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አካታች መሆኑን በመግለጽ፣ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ትልቅ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክክሩ አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን በመጠቆም፣ ሁሉንም ያሳተፈ መሆኑንና በሁሉም ጉዳዮች ላይ በግልጽ እየተወያዩ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ እያካሄድነው ያለው ሀገራዊ ምክክር ለመጭው ትውልድ ደህንነቷ የተጠበቀ እና ሰላሟ የተረጋገጠች ሀገር ለማስረከብ የሚያስችል ነው ያለው ተመካካሪ ደግሞ አብዱላዚዝ አብዲ ነው፡፡ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባት የተፈጠረባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ተስፋ እንዳለውም ተናግሯል።
ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለሀገራዊ መግባባትና ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሰረት እየጣለ ነው 
Aug 5, 2026 193
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለሀገራዊ መግባባትና ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሰረት እየጣለ ነው ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት አብርሃም ጥላሁን ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት፤ የችግሮቻችን ምንጮች ላይ ተቀራርበን አለመወያየታችን ብዙ ዕድሎች እንዲያመልጡን አድርጓል ብሏል። በምክክሩ ላይ በመሳተፍ የሌላውን እይታ መረዳት መቻሉን የገለጸው ወጣቱ፤ መሰል ምክክር የሀገረ መንግሥት ግንባታ እንዲጠናከር መሰረት የሚጥል መሆኑን ተናግሯል። ሀገር የሚገነባው በኃይል ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ ምክክር መሆኑን ገልጾ፤ ''ሂደቱን አሁን ጀምረናል፤ በዚህ ደግሞ ጥሩ ውጤት እንደሚመጣ እምነቴ የጸና ነው'' ሲል ተናግሯል። ሌላው ተመካካሪ አቶ ደሱ ተፈራ በበኩላቸው፤ በዚህ ታሪካዊ የምክክር ሂደት ላይ በመሳተፋቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በአንድ ሀገር ጉዳይ ላይ መምከራቸው ብሩህ ተስፋ የሚፈነጥቅ መሆኑን ጠቅሰው፣ በሀገር ደረጃ የመጀመሪያ የሆነው የምክክር ጉባኤው ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምክክሩ ኢትዮጵያውያን እርስ በእርስ እንዲተዋወቁና እንዲግባቡ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቅሰው፤ ይህ ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። ሌላው የምክክሩ ተሳታፊ አቶ አድጎልኝ መኮንን በሰጡት አስተያየት፤ በምክክር ሂደቱ የሕዝቦችን አንድነት የሚያጠናክሩ ሂደቶችን እየተመለከቱ መሆኑን ጠቁመዋል። የምክክር ሂደቱ እጅግ አበረታች መሆኑን ጠቅሰው፣ ከሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች የተሰበሰቡ ተወካዮች የኢትዮጵያን የጋራ ጥቅም አስቀድመው በጋራ ሲመክሩ መመልከት ትልቅ ደስታና ተስፋ የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምክክሩም ውጤት እያመጣ መሆኑን እስካሁን ከተመለከቱት ሂደት መመልከት መቻላቸውን ጠቅሰው፤ ይህ ለኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የምክክር ጉባኤው በተቀመጠለት መርሀ-ግብር መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል
Aug 5, 2026 201
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018(ኢዜአ)፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተቀመጠለት መርሀ-ግብር መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እየተካሄደ የሚገኘውን የምክክር ጉባኤ አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም ምክክሩ አሁን ላይ በስልታዊ ቡድኖች ደረጃ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተመካካሪዎች ከ10 እና ከ50 አነስተኛ ቡድኖች ተነስተው 250 አባላት ባሏቸው ስልታዊ ቡድኖች ውስጥ የደረሱባቸውን ሀሳቦች አጠናቅረው በማቅረብ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በየደረጃው ያሉ ምክክሮች በቃለ-ጉባኤ ተይዘውና ተፈራርመው ወደ ሚቀጥለው ደረጃ እንደሚሸጋገሩ ያመላከቱት ዋና ኮሚሽነሩ፣ የስልታዊ ቡድኑ ስራ ሲጠናቀቅ ተሳታፊዎቹ ወደ 500 አባላት ዋና ጉባኤ እንደሚሸጋገሩ ገልጸዋል፡፡ ለተመካካሪዎቹም 160 ገደማ አመካካሪዎች እና የተለያዩ የሙያ ዘርፍ ባለሙያዎች እውቀትን መሠረት ያደረገ የተለያዩ ገለጻዎችን እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡ በምክክሩ ላይ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮች፣ ምሁራን፣ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች በእኩል ደረጃ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሁሉም አካላት የሀገርን የጋራ ጥቅም ማዕከል በማድረግ እና የእርስ በእርስ እኩልነትን ባከበረ መልኩ ለምክክሩ ውጤታማነት በጋራ እየመከሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ቃለ-ጉባኤ ያዦቹ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች መሆናቸውንና እያንዳንዷን ነጥብ ለወደፊት ተመራማሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች በሚጠቅም መልኩ በታማኝነት እየሰነዱ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል፡፡ የምክክሩ ሂደቱ በተቀመጠለት መርሃ ግብር መሰረት በጥሩ ሁኔታ እየካሄደ መሆኑንና ሁሉም ወገኖች ሀገራዊ መግባባት ላይ ለመድረስ እየመከሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ተመካካሪዎች የሀሳብ ልዩነቶችን በመሻገር ለኢትዮጵያ በሚበጁ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ነው
Aug 5, 2026 231
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018(ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ተመካካሪዎች ልዩነቶቻቸውን አሻግረው የሀገርን የጋራ ጥቅም በሚያስቀድሙ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። የምክክር ጉባኤው የ250 ስልታዊ ቡድን ውይይት ላይ እንደሚገኝ ዋና ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። 250 ስልታዊ ቡድኖች በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ ባነሷቸውን ሀሳቦች በመነጋገር ቃለ ጉባኤ ይዘው መፈራረም መጀመራቸውን ተናግረዋል። የመፈራረሙ ሂደት ዛሬ የሚጠናቀቅ ከሆነ የ500 ጉባኤው ነገ እንደሚጀመር አመልክተዋል። ስልታዊ ቡድኖቹ በሀሳቦች ላይ የሚያደርጉት ውይይት ከዛሬ የሚያልፍ ከሆነ የ500 ጉባኤው የሚጀመርበት ጊዜ እንደሚራዘምም ተናግረዋል። በቡድኖቹ ውይይቶች ወቅት የተነሱ ሀሳቦች በአመዛኙ ወደ መግባባት የሚወስዱ መሆናቸውን ጠቅሰው አንዳንዳድ ሀሳቦች በደንብ ማጥራትን እንደሚጠይቁ ተናግረዋል። ተመካካሪዎች የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሯቸውም ትልቁን የኢትዮጵያን ምስል በማየት እየተወያዩ እንደሚገኝና የተሰጣቸውን ሚና በሚገባ እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በተያዘለት ጊዜ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እየተካሄደ ይገኛል።
ባለፉት ዓመታት በተካሄደው ዘርፈ ብዙ ሪፎርም አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል-አቶ አደም ፋራህ
Aug 5, 2026 239
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 29 /2018 (ኢዜአ)፦ባለፉት ዓመታት በተካሄደው ዘርፈ ብዙ ሪፎርም አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንትና የዋና ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለፁ። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ትውውቅ መድረክ ተካሂዷል፡፡   የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንትና የዋና ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በፓለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ እና በዲፕሎማሲ ዘርፎች ሰፋፊ የሪፎርም ስራዎች በመከናወናቸው አመርቂ ውጤቶች ተመዝግቧል፡፡ በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር የሚፈጥረውን መደላድል በመጠቀም ከሪፎርም ወደ ተሟላ የፖለቲካ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ትግበራን ለማሳካት እንደሚሰራም ገልጸዋል፡፡ ጽንፈኝነትን በመታገልና የትስስር ትርክት እንዲጎለብት ለማድረግ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማትን ለመፍጠር የተጀመሩ የስታንዳርዳይዜሽን ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ጠቅሰዋል፡፡   በብልጽግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ጠንካራ መንግስት እና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ የፓርቲ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን አቶ አደም አብራርተዋል፡፡ አያይዘውም አመራሩንና አባሉን ጨምሮ ሁሉንም መዋቅር በማነቃነቅ ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተከናውነዋልም ነው ያሉት፡፡ በየደረጃው ያለው አመራርና አባል የተሰጠውን ሃላፊነት በጥራትና በውጤታማነት መፈጸም እንደሚገባው የገለጹት አቶ አደም የጽ/ቤቱ አመራርና ሰራተኛም በበጀት ዓመቱ ለተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡
የምክክር ጉባዔው በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው 
Aug 5, 2026 222
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያሳተፈና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ሲሉ የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ሳዶ ገለጹ። የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። የምክክር መድረኩ ከተለምዷዊና ጊዜያዊ የፖለቲካ ድርድሮች በላቀ፣ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ከልብ እንዲወያዩና መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በሰለጠነ መንገድ እንዲመካከሩ በርን የከፈተ ነው። ሂደቱም የዜጎችን እውነተኛ ሐሳብ በማዳመጥና በጋራ እሴቶች ላይ በመመስረት፣ ባለፉት ዘመናት የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የመደማመጥ ባህልን እየገነባ ይገኛል። በተጨማሪም አስተማማኝና ዘላቂ የሆነ ሀገራዊ ሰላምን በመገንባት የሕግ የበላይነትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ጠንካራ መሠረት እንዲኖረው ከፍተኛ አስተዋጽኦን ያበረክታል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ሳዶ፤ የምክክር ጉባዔው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያሳተፈና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረ ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገርን ለመገንባትና ዘላቂ ዕድገትን ለማረጋገጥ እንዲሁም አስተማማኝ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት እርስ በእርስ ከሚገፋፋ የፖለቲካ አካሄድ በመውጣት፣ ውይይትና የእርስ በእርስ መተማመን አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። መድረኩ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በአንድ ቦታ በማገናኘቱ፣ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረና ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ብለዋል። "ሰላም ከራስ አዕምሮና ከቤተሰብ ይጀምራል" ያሉት አቶ ጁነዲን፤ የራሳችንን ችግር በራሳችን መፍታት እንጂ የውጭ አካላትን መጠበቅ አስፈላጊ አይደለም ሲሉም አመልክተዋል። ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ መደማመጥ፣ መቻቻልና መመካከር ለሁሉም ነገር ቁልፍ መሆኑን መገንዘብ ይገባል ያሉት አቶ ጁነዲን የምክክር መድረኩ ችግሮችን በውይይት የመፍታት ባህልን እንደሚያመጣም እምነታቸው መሆኑን አስታውቀዋል።
ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና መግባባት መሠረትን በማኖር ለትውልዱ የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ ያስችላል
Aug 5, 2026 242
አዳማ፤ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ):-የምክክር ጉባኤው ለዘላቂ ሰላምና መግባባት መሠረትን በማኖር ለትውልዱ የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ እንደሚያስችል ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዳማ ከተማ ሀደ ሲንቄና የሀገር ሽማግሌዎችና ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በዋናነት ለዘመናት የቆዩና ለተለያዩ አለመግባባቶች ምክንያት የሆኑ መሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በዜጎች መካከል ግልጽ፣ አካታችና ውጤታማ ውይይት እንዲደረግ መድረክ አመቻችቷል፡፡ በውይይቱ የሚነሱ አጀንዳዎችና የሚደረሱ ስምምነቶች የሀገሪቱን ዘላቂ ልማት፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማጠናከር እና ለመጪው ትውልድ የተረጋጋችና በጋራ እሴቶች ላይ የተመሠረተች ሀገርን ለማስረከብ መሠረታዊ ሚናን ይጫወታሉ። ጉባዔውን በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ሀደ ስንቄና የሀገር ሽማግሌዎች፤ ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና መግባባት መሠረትን በማኖር ለትውልዱ የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ ያስችላል ብለዋል። የሀገር ሽማግሌ እና የባህል ፍርድ ቤት ዳኛ ድሪባ ጫላ፣ የምክክሩ ጉባኤ ሀገርን ከምንም በላይ በማስቀደም ዘላቂ ሰላምና አንድነትን ለማረጋገጥ መሠረት እንደሚያኖር ገልጸዋል። በምክክሩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ተመካካሪዎች ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የሕዝብ ተወካዮች እንደመሆናቸው መጠን ሙሉ ውክልና እንዳላቸው አመልክተዋል። ተመካካሪዎቹ ከብሔር፣ ከዘር፣ ከሃይማኖትና ከፖለቲካ የጸዳ አቋም በመያዝ ለሀገርና ለሕዝብ የሚበጅ መፍትሔ ያስገኛሉ የሚል ተስፋ መሰነቃቸውንም ተናግረዋል። ሀደ ስንቄ ዘውዴ ከበደ በበኩላቸው፤ ሀደ ስንቄዎች የሰላም፣ የፍቅር እና የእርቅ ተምሳሌት መሆናቸውን ጠቁመው፣ ሁሉም ዜጋ ከዚህ እሴት በመማር በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ሰላምና የሀገር አንድነትን ሊያስቀድም ይገባል ብለዋል። የምክክሩ ጉባኤ ሀደ ስንቄዎችን ጨምሮ የሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮችን በጋራ ማሳተፉ ሀገራችንን ወደ ትክክለኛው ምዕራፍ ለማሸጋገር ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል። የምክክሩ ጉባኤ ለመጪው ትውልድ ብሩህ ተስፋ ያላትንና የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነም አስረድተዋል። "እርስ በርስ ከተደጋገፍንና ከተደማመጥን ልንፈታው የማንችለው ሀገራዊ ችግር የለም" ያሉት ደግሞ የሀገር ሽማግሌ ፈይሣ መገርሳ ናቸው። አሁን ላይ እየተደረገ ያለው የምክክር ጉባኤ ሀገርን አስቀድሞ በመደማመጥ ለነገው ትውልድ የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ ብቸኛ መፍትሔን ይዞ እንደሚመጣ ተስፋ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም ምክክሩ የሁሉም ድምፅና ፍላጎት የሚንፀባረቅበት እንደመሆኑ መጠን መተማመን ላይ በመድረስ ሀገርን ለማጽናት ድልድይ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት አጋርተዋል። አስተያየት ሰጪዎቹ በምክክር መድረኩ ላይ የሚነሱ ጉዳዮች በሀገሪቱ አስተማማኝ መግባባትን ያመጣሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸውም አስታውቀዋል።  
ፖለቲካ
የምክክር ጉባዔው ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ዕድል የፈጠረ ነው
Aug 5, 2026 198
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ዕድል የፈጠረ መሆኑን የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛል። በብሪታንያ እና በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባቶች እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር የጋራና አካታች በመሆኑ ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው።   በብሪታኒያ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባት ኡስታዝ ሙክታር ጀማል እንዳሉት በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር ኢትዮጵያ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ያስፈልጋት የነበረ ታላቅ እርምጃ ነው። ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ኢትዮጵያን ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ሂደት ነው ብለዋል። በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የዳያስፖራ ማህበረሰብ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪ የሃይማኖት አባት ፓስተር አረጋ ሽፈራሁ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አካታችና አሳታፊ መሆኑንና እያንዳንዱ ተመካካሪ ሃሳቡን ያንፀባረቀበት ሁሉም በኢትዮጵያ ልማት፣ ሰላምና ልማት እየመከረ ይገኛል ብለዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ማስረከብ የሚያስችል ነው
Aug 5, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ የሚያስችል ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ስምንት የምክክር አጀንዳዎችን በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የምክክር ጉባዔ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው ምክክር አራት ሺህ ተመካካሪዎች እየመከሩ ይገኛሉ። በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ ያሉ ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ያስችላል። የምክክር ሂደቱ ሁሉም ዜጋ ለሀገሩ የድርሻውን የሚያበረክትበት ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን በመግለጽ፣ ለሀገር ግንባታ የሚረዱ ሀሳቦችን እያንሸራሸሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ተመካካሪ ከተማ ባህሩ እንደገለጹት፣ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው በአጀንዳዎች ዙሪያ ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ጠንካራ መድረክ ሆኖ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ መድረኩ የሀሳብ ብዝሃነትን በአግባቡ የሚያስተናግድና ሁሉም ተመካካሪዎች ሃሳባቸውን በነጻነት እንዲያንሸራሽሩ ሰፊ ዕድል ያመቻቸ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በመሆኑም ሂደቱ ሁሉንም የህብረተሰቡን ክፍሎች ያሳተፈና አካታች በመሆኑ ለሀገራዊ አንድነትና ውይይት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ተመካካሪ እቴነሽ ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አካታች መሆኑን በመግለጽ፣ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ትልቅ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክክሩ አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን በመጠቆም፣ ሁሉንም ያሳተፈ መሆኑንና በሁሉም ጉዳዮች ላይ በግልጽ እየተወያዩ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ እያካሄድነው ያለው ሀገራዊ ምክክር ለመጭው ትውልድ ደህንነቷ የተጠበቀ እና ሰላሟ የተረጋገጠች ሀገር ለማስረከብ የሚያስችል ነው ያለው ተመካካሪ ደግሞ አብዱላዚዝ አብዲ ነው፡፡ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባት የተፈጠረባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ተስፋ እንዳለውም ተናግሯል።
ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለሀገራዊ መግባባትና ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሰረት እየጣለ ነው 
Aug 5, 2026 193
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለሀገራዊ መግባባትና ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሰረት እየጣለ ነው ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት አብርሃም ጥላሁን ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት፤ የችግሮቻችን ምንጮች ላይ ተቀራርበን አለመወያየታችን ብዙ ዕድሎች እንዲያመልጡን አድርጓል ብሏል። በምክክሩ ላይ በመሳተፍ የሌላውን እይታ መረዳት መቻሉን የገለጸው ወጣቱ፤ መሰል ምክክር የሀገረ መንግሥት ግንባታ እንዲጠናከር መሰረት የሚጥል መሆኑን ተናግሯል። ሀገር የሚገነባው በኃይል ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ ምክክር መሆኑን ገልጾ፤ ''ሂደቱን አሁን ጀምረናል፤ በዚህ ደግሞ ጥሩ ውጤት እንደሚመጣ እምነቴ የጸና ነው'' ሲል ተናግሯል። ሌላው ተመካካሪ አቶ ደሱ ተፈራ በበኩላቸው፤ በዚህ ታሪካዊ የምክክር ሂደት ላይ በመሳተፋቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በአንድ ሀገር ጉዳይ ላይ መምከራቸው ብሩህ ተስፋ የሚፈነጥቅ መሆኑን ጠቅሰው፣ በሀገር ደረጃ የመጀመሪያ የሆነው የምክክር ጉባኤው ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምክክሩ ኢትዮጵያውያን እርስ በእርስ እንዲተዋወቁና እንዲግባቡ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቅሰው፤ ይህ ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። ሌላው የምክክሩ ተሳታፊ አቶ አድጎልኝ መኮንን በሰጡት አስተያየት፤ በምክክር ሂደቱ የሕዝቦችን አንድነት የሚያጠናክሩ ሂደቶችን እየተመለከቱ መሆኑን ጠቁመዋል። የምክክር ሂደቱ እጅግ አበረታች መሆኑን ጠቅሰው፣ ከሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች የተሰበሰቡ ተወካዮች የኢትዮጵያን የጋራ ጥቅም አስቀድመው በጋራ ሲመክሩ መመልከት ትልቅ ደስታና ተስፋ የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምክክሩም ውጤት እያመጣ መሆኑን እስካሁን ከተመለከቱት ሂደት መመልከት መቻላቸውን ጠቅሰው፤ ይህ ለኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የምክክር ጉባኤው በተቀመጠለት መርሀ-ግብር መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል
Aug 5, 2026 201
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018(ኢዜአ)፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተቀመጠለት መርሀ-ግብር መሠረት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እየተካሄደ የሚገኘውን የምክክር ጉባኤ አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም ምክክሩ አሁን ላይ በስልታዊ ቡድኖች ደረጃ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተመካካሪዎች ከ10 እና ከ50 አነስተኛ ቡድኖች ተነስተው 250 አባላት ባሏቸው ስልታዊ ቡድኖች ውስጥ የደረሱባቸውን ሀሳቦች አጠናቅረው በማቅረብ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በየደረጃው ያሉ ምክክሮች በቃለ-ጉባኤ ተይዘውና ተፈራርመው ወደ ሚቀጥለው ደረጃ እንደሚሸጋገሩ ያመላከቱት ዋና ኮሚሽነሩ፣ የስልታዊ ቡድኑ ስራ ሲጠናቀቅ ተሳታፊዎቹ ወደ 500 አባላት ዋና ጉባኤ እንደሚሸጋገሩ ገልጸዋል፡፡ ለተመካካሪዎቹም 160 ገደማ አመካካሪዎች እና የተለያዩ የሙያ ዘርፍ ባለሙያዎች እውቀትን መሠረት ያደረገ የተለያዩ ገለጻዎችን እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡ በምክክሩ ላይ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮች፣ ምሁራን፣ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች በእኩል ደረጃ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሁሉም አካላት የሀገርን የጋራ ጥቅም ማዕከል በማድረግ እና የእርስ በእርስ እኩልነትን ባከበረ መልኩ ለምክክሩ ውጤታማነት በጋራ እየመከሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ቃለ-ጉባኤ ያዦቹ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች መሆናቸውንና እያንዳንዷን ነጥብ ለወደፊት ተመራማሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች በሚጠቅም መልኩ በታማኝነት እየሰነዱ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል፡፡ የምክክሩ ሂደቱ በተቀመጠለት መርሃ ግብር መሰረት በጥሩ ሁኔታ እየካሄደ መሆኑንና ሁሉም ወገኖች ሀገራዊ መግባባት ላይ ለመድረስ እየመከሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ተመካካሪዎች የሀሳብ ልዩነቶችን በመሻገር ለኢትዮጵያ በሚበጁ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ነው
Aug 5, 2026 231
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018(ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ተመካካሪዎች ልዩነቶቻቸውን አሻግረው የሀገርን የጋራ ጥቅም በሚያስቀድሙ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። የምክክር ጉባኤው የ250 ስልታዊ ቡድን ውይይት ላይ እንደሚገኝ ዋና ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። 250 ስልታዊ ቡድኖች በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ ባነሷቸውን ሀሳቦች በመነጋገር ቃለ ጉባኤ ይዘው መፈራረም መጀመራቸውን ተናግረዋል። የመፈራረሙ ሂደት ዛሬ የሚጠናቀቅ ከሆነ የ500 ጉባኤው ነገ እንደሚጀመር አመልክተዋል። ስልታዊ ቡድኖቹ በሀሳቦች ላይ የሚያደርጉት ውይይት ከዛሬ የሚያልፍ ከሆነ የ500 ጉባኤው የሚጀመርበት ጊዜ እንደሚራዘምም ተናግረዋል። በቡድኖቹ ውይይቶች ወቅት የተነሱ ሀሳቦች በአመዛኙ ወደ መግባባት የሚወስዱ መሆናቸውን ጠቅሰው አንዳንዳድ ሀሳቦች በደንብ ማጥራትን እንደሚጠይቁ ተናግረዋል። ተመካካሪዎች የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሯቸውም ትልቁን የኢትዮጵያን ምስል በማየት እየተወያዩ እንደሚገኝና የተሰጣቸውን ሚና በሚገባ እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በተያዘለት ጊዜ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እየተካሄደ ይገኛል።
ባለፉት ዓመታት በተካሄደው ዘርፈ ብዙ ሪፎርም አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል-አቶ አደም ፋራህ
Aug 5, 2026 239
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 29 /2018 (ኢዜአ)፦ባለፉት ዓመታት በተካሄደው ዘርፈ ብዙ ሪፎርም አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንትና የዋና ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለፁ። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ትውውቅ መድረክ ተካሂዷል፡፡   የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንትና የዋና ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በፓለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ እና በዲፕሎማሲ ዘርፎች ሰፋፊ የሪፎርም ስራዎች በመከናወናቸው አመርቂ ውጤቶች ተመዝግቧል፡፡ በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር የሚፈጥረውን መደላድል በመጠቀም ከሪፎርም ወደ ተሟላ የፖለቲካ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ትግበራን ለማሳካት እንደሚሰራም ገልጸዋል፡፡ ጽንፈኝነትን በመታገልና የትስስር ትርክት እንዲጎለብት ለማድረግ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማትን ለመፍጠር የተጀመሩ የስታንዳርዳይዜሽን ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ጠቅሰዋል፡፡   በብልጽግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ጠንካራ መንግስት እና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ የፓርቲ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን አቶ አደም አብራርተዋል፡፡ አያይዘውም አመራሩንና አባሉን ጨምሮ ሁሉንም መዋቅር በማነቃነቅ ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተከናውነዋልም ነው ያሉት፡፡ በየደረጃው ያለው አመራርና አባል የተሰጠውን ሃላፊነት በጥራትና በውጤታማነት መፈጸም እንደሚገባው የገለጹት አቶ አደም የጽ/ቤቱ አመራርና ሰራተኛም በበጀት ዓመቱ ለተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡
የምክክር ጉባዔው በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው 
Aug 5, 2026 222
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያሳተፈና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ሲሉ የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ሳዶ ገለጹ። የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። የምክክር መድረኩ ከተለምዷዊና ጊዜያዊ የፖለቲካ ድርድሮች በላቀ፣ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ከልብ እንዲወያዩና መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በሰለጠነ መንገድ እንዲመካከሩ በርን የከፈተ ነው። ሂደቱም የዜጎችን እውነተኛ ሐሳብ በማዳመጥና በጋራ እሴቶች ላይ በመመስረት፣ ባለፉት ዘመናት የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የመደማመጥ ባህልን እየገነባ ይገኛል። በተጨማሪም አስተማማኝና ዘላቂ የሆነ ሀገራዊ ሰላምን በመገንባት የሕግ የበላይነትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ጠንካራ መሠረት እንዲኖረው ከፍተኛ አስተዋጽኦን ያበረክታል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ሳዶ፤ የምክክር ጉባዔው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያሳተፈና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረ ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገርን ለመገንባትና ዘላቂ ዕድገትን ለማረጋገጥ እንዲሁም አስተማማኝ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት እርስ በእርስ ከሚገፋፋ የፖለቲካ አካሄድ በመውጣት፣ ውይይትና የእርስ በእርስ መተማመን አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። መድረኩ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በአንድ ቦታ በማገናኘቱ፣ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረና ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ብለዋል። "ሰላም ከራስ አዕምሮና ከቤተሰብ ይጀምራል" ያሉት አቶ ጁነዲን፤ የራሳችንን ችግር በራሳችን መፍታት እንጂ የውጭ አካላትን መጠበቅ አስፈላጊ አይደለም ሲሉም አመልክተዋል። ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ መደማመጥ፣ መቻቻልና መመካከር ለሁሉም ነገር ቁልፍ መሆኑን መገንዘብ ይገባል ያሉት አቶ ጁነዲን የምክክር መድረኩ ችግሮችን በውይይት የመፍታት ባህልን እንደሚያመጣም እምነታቸው መሆኑን አስታውቀዋል።
ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና መግባባት መሠረትን በማኖር ለትውልዱ የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ ያስችላል
Aug 5, 2026 242
አዳማ፤ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ):-የምክክር ጉባኤው ለዘላቂ ሰላምና መግባባት መሠረትን በማኖር ለትውልዱ የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ እንደሚያስችል ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዳማ ከተማ ሀደ ሲንቄና የሀገር ሽማግሌዎችና ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በዋናነት ለዘመናት የቆዩና ለተለያዩ አለመግባባቶች ምክንያት የሆኑ መሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በዜጎች መካከል ግልጽ፣ አካታችና ውጤታማ ውይይት እንዲደረግ መድረክ አመቻችቷል፡፡ በውይይቱ የሚነሱ አጀንዳዎችና የሚደረሱ ስምምነቶች የሀገሪቱን ዘላቂ ልማት፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማጠናከር እና ለመጪው ትውልድ የተረጋጋችና በጋራ እሴቶች ላይ የተመሠረተች ሀገርን ለማስረከብ መሠረታዊ ሚናን ይጫወታሉ። ጉባዔውን በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ሀደ ስንቄና የሀገር ሽማግሌዎች፤ ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና መግባባት መሠረትን በማኖር ለትውልዱ የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ ያስችላል ብለዋል። የሀገር ሽማግሌ እና የባህል ፍርድ ቤት ዳኛ ድሪባ ጫላ፣ የምክክሩ ጉባኤ ሀገርን ከምንም በላይ በማስቀደም ዘላቂ ሰላምና አንድነትን ለማረጋገጥ መሠረት እንደሚያኖር ገልጸዋል። በምክክሩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ተመካካሪዎች ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የሕዝብ ተወካዮች እንደመሆናቸው መጠን ሙሉ ውክልና እንዳላቸው አመልክተዋል። ተመካካሪዎቹ ከብሔር፣ ከዘር፣ ከሃይማኖትና ከፖለቲካ የጸዳ አቋም በመያዝ ለሀገርና ለሕዝብ የሚበጅ መፍትሔ ያስገኛሉ የሚል ተስፋ መሰነቃቸውንም ተናግረዋል። ሀደ ስንቄ ዘውዴ ከበደ በበኩላቸው፤ ሀደ ስንቄዎች የሰላም፣ የፍቅር እና የእርቅ ተምሳሌት መሆናቸውን ጠቁመው፣ ሁሉም ዜጋ ከዚህ እሴት በመማር በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ሰላምና የሀገር አንድነትን ሊያስቀድም ይገባል ብለዋል። የምክክሩ ጉባኤ ሀደ ስንቄዎችን ጨምሮ የሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮችን በጋራ ማሳተፉ ሀገራችንን ወደ ትክክለኛው ምዕራፍ ለማሸጋገር ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል። የምክክሩ ጉባኤ ለመጪው ትውልድ ብሩህ ተስፋ ያላትንና የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነም አስረድተዋል። "እርስ በርስ ከተደጋገፍንና ከተደማመጥን ልንፈታው የማንችለው ሀገራዊ ችግር የለም" ያሉት ደግሞ የሀገር ሽማግሌ ፈይሣ መገርሳ ናቸው። አሁን ላይ እየተደረገ ያለው የምክክር ጉባኤ ሀገርን አስቀድሞ በመደማመጥ ለነገው ትውልድ የተረጋጋች ሀገርን ለማስረከብ ብቸኛ መፍትሔን ይዞ እንደሚመጣ ተስፋ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም ምክክሩ የሁሉም ድምፅና ፍላጎት የሚንፀባረቅበት እንደመሆኑ መጠን መተማመን ላይ በመድረስ ሀገርን ለማጽናት ድልድይ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት አጋርተዋል። አስተያየት ሰጪዎቹ በምክክር መድረኩ ላይ የሚነሱ ጉዳዮች በሀገሪቱ አስተማማኝ መግባባትን ያመጣሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸውም አስታውቀዋል።  
ማህበራዊ
በሆስፒታሉ የኦክስጅን ማምረቻ ማዕከልን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎት መስጫዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረጉ
Aug 5, 2026 137
ባህርዳር ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ በባህር ዳር ከተማ ፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተገነባ የኦክስጅን ማምረቻ ማዕከልን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎት መስጫዎች የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረጉ። በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱን ጨምሮ ሌሎች የዘርፉ የስራ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን የሆስፒታሉ የስራ እንቅስቃሴም ተጎብኝቷል ። በሆስፒታሉ ከኦክስጅን ማምረቻ ማዕከል በተጨማሪ የጨቅላ ህፃናት ህክምና ማዕከልና የዲጂታል ቋት ምረቃ የተካሄደ ሲሆን የተለያዩ አገልግሎቶችና የቀዶ ህክምና ክፍል የእድሳት ማስጀመሪያ ስነ ስርአት ተከናውኗል።   በሆስፒታሉ የኦክስጅን ማምረቻ ማዕከል መገንባት የህክምና አገልግሎት አሰጣጡን የተሟላ እንደሚያደርገው የሆስፒታሉ የባዮ ሜዲካል ክፍል አስተባባሪ ውዴ በቀለ ለኢዜአ ገልፀዋል። ማእከሉ በአመት 28ሺህ 800 ሲሊንደር ኦክሲጅን የማምረት አቅም እንዳለው ጠቁመው ይህም ምርቱን ከሆስፒታሉ ባለፈ ለሌሎች በአካባቢው ለሚገኙ ጤና ተቋማት የማቅረብ አቅም እንደሚኖረው አመላክተዋል ። በስነ ስርአቱ የችግኝ ተከላ ተካሂዷል። በነገው እለትም ሚኒስትሯ በተገኙበት በጤናው ዘርፍ የሚመክር መድረክ በባህር ዳር ከተማ እንደሚካሄድ ተመላክቷል።
የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር ለማዘመን የተጀመሩ ተግባራት ኑሯችንን ቀይረውልናል - የሞዴል መንደር ተጠቃሚዎች 
Aug 5, 2026 202
ሚዛን አማን፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦መንግስት የገጠሩን ማህበረሰብ የአኗኗር ሥርአት ለማዘመን የጀመራቸው ተግባራት ኑሯቸውን እንደቀየረው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የገጠር ሞዴል መንደር ተጠቃሚዎች ገለጹ። በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር ደምባሶ ወይሳ ፤ መንግስት የገጠሩን ማህበረሰብ የአኗኗር ሥርአት ለማዘመን የጀመራቸው ሥራዎች የኑሮ ዘይቤያቸውን እንደቀየረው ገልጸዋል።   ከዚህ ቀደም ከቤት እንስሳት ጋር በአንድ ቤት ውስጥ ይኖሩ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት የሞዴል መንደሩን ግንባታ ተከትሎ የሰውና የእንስሳት መኖሪያ በተለየበት ሁኔታ በዘመናዊ ቤት መኖር እንደጀመሩ ተናግረዋል። ይህም የግልና የአካባቢ ንጽህናን ለመጠበቅ እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ አርሶ አደር ከድር ጋንታ፤ ለጥምር እርሻ ምቹ የሆነ ጓሮ በማግኘታቸው በኢኮኖሚ የተሻለ ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ጠቁመዋል።   መንደሩ በዘመናዊ መንገድ እንዲኖሩ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩ ባለፈ የማር፣ የዶሮ፣ የጓሮ አትክልትና ሌሎች የግብርና ሥራዎችን በማከናወን ኑሯቸው እንዲሻሻል በማድረጉ ውጤታማ እንደሆኑ ተናግረዋል።   መንግስት በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ ኢኒሽዬቲቭ ሠርቶ ያስረከበን ቤት አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ እንድንኖር አስችሎናል ያሉት ደግሞ ወይዘሮ አልጋነሽ ሙላቱ የተባሉ ተጠቃሚ ናቸው። በክልሉ የገጠሩን ማኅበረሰብ ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን ናቸው።   በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት 16 የገጠር ሞዴል መንደሮች መገንባታቸውን ገልጸው በተያዘው በጀት ዓመትም በ41 የክልሉ ወረዳዎች ለማስፋፋት ይሰራል ብለዋል፡፡ የገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ ሥራ የገጠር ትራንስፎርሜሽን አካል ሲሆን ሁለንተናዊ ብልጽግናን የማረጋገጥ ግብን ለማሳካት ከሚያስችሉ ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በገጠር ሞዴል መንደር እስካሁን የተገነቡ ቤቶች የአርሶ አደሩን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።   አርሶ አደሩ በጓሮው የሚያመርተው ምግብ ራሱን ከመቻል ባለፈ ለገበያ ጭምር ለማቅረብ ያግዛል ያሉት አቶ ፍቅሬ፣ በሞዴል መንደሩ የገጠርና ከተማ ትስስርን በማሳለጥ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ ይቻላል ብለዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከሰሞኑ ብቻ በቤንች ሸኮ እና ሸካ ዞኖች የተገነቡ አምስት ሞዴል መንደሮች ተገንብተው ለነዋሪዎች ተላልፈዋል።
ሠራዊቱ ሀገርና ሕዝብን ከመጠበቅ ባሻገር ማኅበራዊ ኃላፊነቱን መወጣት መሰረታዊ እሴቱ  ነው
Aug 5, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ሀገርና ሕዝብን ከመጠበቅ ባሻገር በበጎ አድራጎት ተግባራት ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን መወጣት መሰረታዊ እሴቱ እንደሆነ የመከላከያ ሠራዊት የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት በመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር በመገኘት የቁሳቁስ ድጋፍና የማዕድ ማጋራት አካሂደዋል፡፡   በመከላከያ ሠራዊት የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ እንደገለጹት፤ የመከላከያ ሠራዊቱ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራት ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል። በዛሬው ዕለትም በመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኅበር በመገኘት ሁለንተናዊ ድጋፍ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።   ማኅበሩ "ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው" በሚለው መርህ የሚያከናውነው ተግባር የላቀ ሰብአዊነትን የሚያሳይና ለአገር አርአያ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሀገርና የሕዝብ ሰላም ከመጠበቅ ባሻገር ድጋፍ የሚሹ ዜጎችን መርዳት የሠራዊቱ መሠረታዊ እሴት መሆኑን አብራርተዋል። ይህ ሁለንተናዊ ድጋፍ የአንድ ጊዜ ሳይሆን ሁል ጊዜም ከማኅበሩ ጎን በመቆም ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። አረጋውያንንና ሕሙማንን መደገፍ የሁሉም ኃላፊነት መሆን እንደሚገባው ጠቁመው፤ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ባለሀብቶችና በውጭ አገር የሚኖሩ ዜጎች ለዚህ የተቀደሰ ዓላማ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።   በማኅበሩ ለሚገኙ አረጋውያንና ሕሙማንም "እናንተ የአገራችን ባለውለታና የእኛ አደራ ናችሁ፤ ብቻችሁን አይደላችሁም፣ መላው ሠራዊትና ሕዝብ ከእናንተ ጋር ነው" በማለትም መልዕክት አስተላልፈዋል። እርስ በርስ መረዳዳትና መደጋገፍ የኢትዮጵያውያን የቆየ ባህል በመሆኑ፣ ይህንን መልካም እሴት በተግባር በማሳየት አገራዊ አንድነትንና ፍቅርን ማጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል።   የመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ ቢኒያም በለጠ በበኩላቸው፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ለማኅበሩ ላደረገው የቁሳቁስ ድጋፍና ማዕድ ማጋራት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሌሎች ተቋማትና ግለሰቦችም የመከላከያ ሠራዊቱን አርአያ በመከተል ለማኅበሩ የሚችሉትን ድጋፍ ሁሉ እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
የሻደይ በዓልን ባህላዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ዝግጅት ተደርጓል
Aug 5, 2026 142
ሰቆጣ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፡-በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የሻደይ በዓል ባህላዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ዝግጅት መደረጉን የባህል ፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ አስታውቋል። መምሪያው የ2018 ዓ/ም የሻደይ በዓል አከባበር ዙሪያ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል። የመምሪያው ኃላፊ አቶ ይርጋ ማርዬ በመግለጫው ወቅት እንዳሉት የሻደይ በዓል ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የማንነት መገለጫ በዓል ነው ብለዋል። በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በየዓመቱ ነሃሴ አጋማሽ ጀምሮ የሚከበረውን የሻደይ በዓልን ባህላዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ዝግጅት መደረጉን ነው ያስታወቁት። ስልጣኔ ባልተስፋፋበት ዴሞክራሲ ባልሰፈነበት ዘመን የሻደይ በዓል የሴቶችን ነፃነት በማጎናፀፍ በአደባባይ ወጥተው ባህላቸውን እንዲያከብሩ ያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል። የዘንድሮው የሻደይ በዓልን "ሻደይን እናከብራለን እሴቶቻችንን እንጠብቃለን" በሚል መሪ ቃል ከነሃሴ 15ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በደመቀ መልኩ በሰቆጣ ከተማ እንደሚከበር ገልፀዋል። ሻደይን በአደባባይ ከማክበር ጎን ለጎንም የብሄረሰቡን የባህልና ቋንቋ ጥናት ዙሪያ የፓናል ውይይትን ጨምሮ የንግድ ኢግዚቢሽንና በሌሎች መርሃ ግብሮች እንደሚከናወኑም ጠቁመዋል። የሻደይ በዓል ላይ የዋግን የቱሪዝም መዳረሻዎችን የማስተዋወቅ ስራ ይከናወናል ያሉት አቶ ይርጋ በክልሉና በፌዴራሉ መንግስት የተገነቡ መሰረተ ልማቶች እንደሚመረቁም ተናግረዋል። ሻደይ በዓልን ባህላዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር አስፈላጊ የሆነ ዝግጅት መደረጉንም ነው የተናገሩት።
ኢኮኖሚ
የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በኦንላይን ክፍያ መፈጸም ይጠበቅባቸዋል
Aug 5, 2026 261
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ መልዕክት የደረሳቸው የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በኦንላይን ክፍያቸውን በመፈጸም የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቀረበ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰውነት አየለ በሰጡት መግለጫ፣ቢሮው የግብር ስርዓቱን በማዘመን እና ፍትሃዊ አሰባሰብን በመዘርጋት ገቢን በጥራት እየሰበሰበ ይገኛል ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ ከሚሰበስበው ገቢ 72 በመቶውን ለዘላቂ ልማት፣ ለሰው ተኮር ፕሮጀክቶች እና ለኮሪደር ልማት በማዋል የመዲናዋን ገጽታና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እያጎለበተ ይገኛልም ብለዋል። በከተማዋ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ ከ456 ሺህ በላይ የደረጃ «ለ» ግብር ከፋዮች አዲስ በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ መሰረት ግዴታቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ከደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች በዘንድሮ በጀት ዓመት 9.2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል። መረጃቸው ለተሟላላቸው ግብር ከፋዮች የግብር ውሳኔ በስልክ የጽሁፍ መልዕክት የተላከ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ ግብራቸውን በወቅቱ መክፈላቸውን አንስተዋል። እስከ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም መልዕክት የደረሳቸው ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በኦንላይን በመክፈል ከቅጣት እና ወለድ ራሳቸውን መጠበቅ ይኖርባቸዋል ብለዋል። በተለያዩ ምክንያቶች መልዕክት ያልደረሳቸው ወይም ከሐምሌ 25 በኋላ የደረሳቸው ግብር ከፋዮች መልዕክቱ ከተላከላቸው ጊዜ ጀምሮ እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ ያለ ቅጣት ግብራቸውን መክፈል እንደሚችሉ አስታውቀዋል።
የባህር በር የዚህ ትውልድ ብሔራዊ አጀንዳ ነው
Aug 5, 2026 170
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የባህር በር የዚህ ትውልድ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑን የማህበራዊ ሳይንስ ምሁር ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ በታሪክም ሆነ ህጋዊ መሰረትን በካደ ሁኔታ ያጣችው የባህር በር ኢኮኖሚያዊ ዕድገቷን እንደጎዳው ምሁራን ያስረዳሉ። ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት እንድትሆንና ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር ላይ የተሄደበትን ርቀት አስመልክቶ ኢዜአ ከማህበራዊ ሳይንስ ምሁሩ ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር ) ጋር ቆይታ አድርጓል። ምሁሩ በቆይታቸው እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ታሪካዊ፣ ጂኦ-ፖለቲካዊና ህጋዊ መሰረትን የተከተለ ነው። በውጭ ኃይሎች ሴራና በሀገር ውስጥ በነበሩ ውስብስብ ችግሮች ምክንያት ሀገሪቱ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነት ለማስመለስ የጀመረችው ህጋዊና ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ወቅታዊ መሆኑን ጠቁመዋል። ዓለም አቀፍ የባህር ህግ ወደብ የሌላቸው ሀገራት ወደ ባህር የመድረስና የመጠቀም መብታቸውን በግልፅ እውቅና ይሰጣል ብለዋል። ይህም ሀገራት ብሔራዊ ጥቅማቸውን ለማስከበርና የባህር በር ለማግኘት ለሚያደርጉት ዲፕሎማሲያዊና ህጋዊ ጥረት ትልቅ መሰረት ነው ሲሉ አክለዋል። ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን በሴራ ብታጣም ዳግም የባህር በር ባለቤት ለመሆን የጀመረችው ጥረት የህግና የታሪክ መሰረት ያለው መሆኑን አስረድተዋል። የባህር በር ጥያቄው የኢትዮጵያን የንግድ ሚዛን ከማስጠበቅ ባሻገር፣ ለአፍሪካ ቀንድ ቀጣና የጋራ ተጠቃሚነትና አስተማማኝ ሰላም የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለውም ብርሃኑ (ዶ/ር ) አክለዋል። ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባህር በር ማግኘቷ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚኖራትን የንግድና የኢኮኖሚ ትስስር በማሳደግ ቀጠናዊ ውህደትን ያፋጥናል ሲሉም ገልጸዋል። ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) የባህር በር የትውልድ ብሔራዊ ህልውና ጉዳይ መሆኑንም ገልጸዋል። ለተግባራዊነቱም ዜጎች የፖለቲካም ሆነ ሌሎች አመለካከት ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን በመተው ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም በጋራ መቆም አለባቸው ብለዋል። መንግስት በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መርህ የጀመረውን ጥረት ለማሳካት የሕዝብ ዲፕሎማሲ ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል ሲሉም አመልክተዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የዘርፉ ምሁራን የባህር በር ለማግኘት የተጀመረውን ሀገራዊ ጥረት በምርምር፣ በታሪካዊና በህጋዊ ሰነዶች በማስደገፍ ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ መክረዋል። የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ለማስከበርና የባህር በር ባለቤትነትን እውን ለማድረግ አሁን የተጀመሩት ሁሉን አቀፍ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ምሁሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በክልሉ የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር የኑሮ ጫናን ለማቃለል ትኩረት ተደርጓል
Aug 5, 2026 202
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፡-በክልሉ በተያዘው የበጀት ዓመት የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር እንዲሁም የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦት እንዲሻሻል በማድረግ የኑሮ ጫናን ለማቃለል በትኩረት እንደሚሰራ የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ። የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ በበጀት አመቱ በሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ላይ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በያዝነው የበጀት አመት በክልሉ የኑሮ ጫናን ለማቃለል የሚያስችሉ ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ይከናወናሉ ብለዋል። በተለይም የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦት እንዲሻሻል የማድረግ ስራዎች የላቀ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል። ሸማቹን ማህበረሰብ ለአላስፈላጊ ወጪና ለእንግልት የሚዳርጉ ሰው ሰራሽ የዋጋ ጭማሪዎች የሚያደርጉ ነገዴዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ የማድረግ ስራ ይሰራል ነው ያሉት። የምርት አቅርቦትን በማሻሻል፣ የገበያ ሰንሰለት ማነቆዎችን በመፍታትና ህገ-ወጥ ንግድን የመቆጣጠር ስራዎችም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ጠቁመዋል። የቅዳሜና እሁድ ገበያን በማጠናከር የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችና የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በቀጥታ ለሸማቹ በማቅረብ የኑሮ ጫናን ለማቃለል እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በምዕራብ ጎንደር ዞን በመኸር እርሻ 546 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለምቷል
Aug 5, 2026 208
ገንዳውኃ፣ ሐምሌ29/2018 (ኢዜአ):- በምዕራብ ጎንደር ዞን በመኸር እርሻ546 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በዞኑ ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ሞገስ ጋሹ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በምርት ዘመኑ በዞኑ ከ529 ሺህ 650 ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል። በተደረገው ከፍተኛ ርብርብም እስካሁን ባለው ሂደት ከእቅድ በላይ ከ546 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የተለያዩ ሰብሎችን ማልማት እንደተቻለ ተናግረዋል። ከዚሁ ውስጥ ከ98 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው መሬት በባለሀብቶች የለማ ሲሆን፣ ቀሪው ደግሞ በአርሶ አደሮች መሸፈኑን ገልጸዋል። አኩሪ አተር፣ ማሽላ፣ ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ማሾና ሌሎች ሰብሎች በብዛት የለሙ መሆናቸውንም አመልክተው፤ በምርት ዘመኑ ከለማው መሬት ከ12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የተጀመረው እምቅ የልማት እንቅስቃሴ እስከ ምርት ስብሰባ ድረስ ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግለት ጠቁመዋል። በዞኑ በእርሻ ኢንቨስትመንት ከተሰማሩ ባለሀብቶች መካከል አቶ አብርሃም ድንቁ እንዳሉት፤ በዘንድሮው ዓመት ግብዓት እና የባለሙያ ድጋፍን በወቅቱ በማግኘታቸው የልማት ሥራዎችን በስፋት ማከናወን አስችሏቸዋል። በዚህም 200 ሄክታር መሬት በጥጥ፣ ማሽላ፣ አኩሪ አተርና ሰሊጥ ማልማታቸውን አመልክተው፤ ሰብሉ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ትራክተሮችንና ሌሎች የግብርና ሜካናይዜሽን መሣሪያዎችን በስፋት በመጠቀማቸው ያቀዱትን መሬት በፍጥነት በዘር ለመሸፈን እንደቻሉም አብራርተዋል። በመተማ ወረዳ በግብርና ሥራ የሚተዳደሩት አርሶ አደር ብርሃኑ ጌታሁን በበኩላቸው፤ በመኸር እርሻው 15 ሄክታር መሬታቸውን ሙሉ ለሙሉ ማልማታቸውን ገልጸዋል። "የዝናብ ወቅቱን ጠብቀን በኩታ ገጠም አሰራር ነው መሬታችንን ያረስነው" ያሉት አርሶ አደሩ፤ የዝናብ ሥርጭቱን መሠረት ያደረገ የተባይና አረም ቁጥጥር እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። አሁን የተዘራው ሰብል ተስፋ ሰጪ በመሆኑ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁም ገልጸዋል። በዞኑ ባለፈው የ2017/18 የምርት ዘመን 525 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለምቶ ከ10 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደተገኘ ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት ያሳያል 
Aug 5, 2026 207
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን የቤኒን የዲጂታል ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን ገለጹ፡፡ በቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የተመራ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ የአምስት ቀን የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ መግባቱ ይታወቃል።   በዚህም መሰረት ሚኒስትሩና የልዑካን ቡድናቸው በኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትና በፋይዳ ቨርስ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ፈጣን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግር እየተደረገ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን በአጭር ጊዜ አስገራሚ የዲጂታል መሰረተ ልማት በመገንባትና ፈጣን የመንግሥት አገልግሎት ስርዓት ላስመዘገቡት ዕምርታ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያና ቤኒን መካከል ያለው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክፍተት በጋራ መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ልምድ መለዋወጥ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት በግልጽ እንደሚያሳይ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በዲጂታል መሰረተ ልማት እያደገች መሆኑን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ከዚህ መማር አጀንዳችንን ለማቀላጠፍ ያግዘናል ብለዋል፡፡ ቤኒን በሳይበር ደህንነት ያላትን ጠንካራ አቅም ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለማሳደግ በአቅም ግንባታና በዕውቀት ልውውጥ በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡ የፋይዳ ቨርስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮዳሔ አርዓያሥላሴ በበኩላቸው፤ የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ለኢትዮጵያ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል፡፡   የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ለዲጂታል ዲፕሎማሲ አቅም ግንባታ የጎላ አበርክቶ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ብዙ የተለመደው ከአውሮፓ ወይም ከኤዥያ የሚመጣን ስርዓት ማስተዳደር ነው ያሉት አቶ ዮዳሔ፤ ቴክኖሎጂን በራስ አቅም መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ሁሉም መገንዘቡን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የራሷን ቴክኖሎጂዎች በማፍለቅ ለሌሎች ትምህርት መስጠቷ አፍሪካውያን በራሳቸው እንዲተማመኑና ዕምነት እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ስያሜውንና ተልዕኮውን በመቀየር ራሱን ችሎ የመንግሥት የልማት ድርጅት ሆኖ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥር መካተቱን አንስተዋል፡፡ ይሄውም አገልግሎቱን ከኢትዮጵያ ውጪ በማስፋት በአፍሪካ ሀገራት ጭምር የማማከርና ስርዓት የመገንባት ዕድሎችን የምናገኝበት ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ የኢፌዴሪ የመሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ አለማየሁ፤ መሶብ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን አሻሽሏል ብለዋል፡፡   በኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ 108 የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በመክፈት ከ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ማገልገል ተችሏል ብለዋል፡፡ ከ220 በላይ አገልግሎቶችን በላቀ ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊ አሰራር በመስጠት የተገልጋዮችን እርካታ 98 በመቶ ማድረስ እንደተቻለም ገልጸዋል፡፡ መሶብ የኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የመሻገር ህልም መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ ሀገራት ልምድ የሚወስዱበትና የዲፕሎማሲ ተግባቦት የሚፈጠርበት ነው ብለዋል፡፡ የቤኒን ብቻ ሳይሆን የሌሎች ዓለም ሀገራት ጭምር አይተው የሚደነቁበት መሆኑን በማንሳት ጉብኝቱ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ብዙ ርቀት መጓዟን እንደሚያሳይ ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን ኢንጂነሮችና በኢትዮጵያ ሀብት የለማ መሆኑ ኢትዮጵያውያን እውቀትና አቅማችንን አስተባብረን መስራት እንደምንችል አሳይቷል ብለዋል፡፡
ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት አስተማማኝ የልኬትና የካሊብሬሽን ሥርዓት መገንባት ወሳኝ ጉዳይ ነው - ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)
Aug 5, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት አስተማማኝ የልኬትና የካሊብሬሽን ሥርዓት መገንባት ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ። 19ኛው የአፍሪካ ሥነ-ልክ ድርጅት (ሜትሮሎጂ) ጠቅላላ ጉባዔ "ሥነ-ልክ ለዲጂታል ሽግግር፤ ተዓማኒ ልኬቶች ለአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።   በጠቅላላ ጉባዔው የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሙሉጌታ ደርበው (ዶ/ር) እና የአፍሪካ ሥነ-ልክ ድርጅት (AFRIMETS) ፕሬዚዳንት ሔነሪ ኪበት ሮቲች (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ የዘርፉ ተወካዮች ተገኝተዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በአንድ የአፍሪካ ሀገር የተመረቱ ምርቶች ተደራራቢ የጥራትና የልኬት ፍተሻዎችን አልፈው ወደ ሌላ ሀገር በነፃነት እንዲዘዋወሩ የተቀናጀ የልኬት ስታንዳርድ መዘርጋት አስፈላጊ ነው።   አህጉራዊ የንግድ ትስስሩ ውጤታማ ሊሆን የሚችለውም ሀገራት ወጥና ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የልኬት ቁጥጥር ሥርዓት ሲኖራቸው እንደሆነ አስረድተዋል። አክለውም የሜትሮሎጂ ሥርዓትን ማዘመንና ዲጂታላይዝ ማድረግ አፍሪካ ለሰው ሠራሽ አስተውሎት እና ለላቀ ማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂዎች ዝግጁ እንድትሆን እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ከመደበኛ የሥነ-ልክ ሥርዓቶች ጋር በማጣመር የላቦራቶሪ ምርመራ ውጤቶች አህጉራዊ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ማድረግ የንግድ እንቅፋቶችን እንደሚያስወግድም ጠቁመዋል። የላቦራቶሪ ምርመራዎችንና የካሊብሬሽን አቅምን ማሳደግ የንግድ እንቅፋቶችን ከመቅረፉ ባሻገር፣ አህጉሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር በታማኝ የልኬት መረጃ ለማስደገፍ እንደሚያስችልም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዋ ተቋማዊ አቅምን ለማሳደግ፣ የውጭ ኢንቨስትመንት ለመሳብ እና ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየሰራች መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ አጋሮች ጋር በመተባበር የሜትሮሎጂ ስታንዳርዶችን ለማጠናከርና የአፍሪካን የኢኮኖሚ ትስስር እውን ለማድረግ ሙሉ ቁርጠኝነቷን አረጋግጣለች።  
የቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትን ጎበኙ
Aug 5, 2026 225
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትን ጎብኝተዋል። የቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የተመራ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ የአምስት ቀን የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ መግባቱ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ሚኒስትሩና የልዑካን ቡድናቸው በኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎት ጉብኝት እያደረገ ነው።   በኢፌዴሪ የመሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ አለማየሁ ለልዑኩ ገለፃ አድርገውላቸዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው በገለፃቸው በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ዓመቱ ውስጥ ከ200 በላይ የመንግሥት አገልግሎት በተሟላ መሰረተ ልማት ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ተችሏል ብለዋል። ይህም የኢትዮጵያ ቁልፍ የኢኮኖሚ መሰረተ ልማት እንደሆነ በመግለጽ ቅሬታ የሚበዛበትን የመንግስት አገልግሎት ግልፅና ቀልጣፋ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን በማሳለጥ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። አገልግሎቱ የመንግስት ተቋማትን በማቀናጀት ተቋማት በአንድ ጣሪያ ስር ሁሉንም የመንግሥት አገልግሎት በፍትሐዊነት መስጠት አስችሏል ብለዋል።   የቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና ኢኖቬሽን ሚኒስትሩና ልዑካቸው በቆይታቸው ከመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች ጋር በሁለትዮሽና ትብብርን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ። በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የህዝብ አስተዳደር፣ ኢኖቬሽንና ስትራቴጂያዊ አስተዳደር ላይ ልምድ ይለዋወጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Aug 4, 2026 898
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት ዛሬ የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረውን ፋይዳቨርስን በይፋ ሥራ አስጀምረናል ብለዋል።   ባለፉት ጥቂት ዓመታት የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ወደ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎችን በመመዝገብ፣ ከ160 ሚሊዮን በላይ የማረጋገጫ አገልግሎቶችን በመስጠትና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ የዲጂታል ኢኮኖሚያችን የጀርባ አጥንት መሆኑን አስመስክሯል ነው ያሉት። ዛሬ ደግሞ ይህ ስኬታችን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ተሸጋግሮ፣ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር ፋይዳቨርስ በሚል ስያሜ ራሱን የቻለ የመንግስት የልማት ድርጅት በመሆን ወደ ስራ ገብቷል ብለዋል። ይህ ውሳኔ ዲጂታል ማንነት ልክ እንደ መንገድ፣ ኃይል እና ቴሌኮሙኒኬሽን ሁሉ ለሀገራችን ተወዳዳሪነትና ዘላቂ እድገት ወሳኝ የሆነ ስትራቴጂካዊ ሀገራዊ መሰረተ ልማት መሆኑን ማረጋገጫችን ነው ሲሉ ገልጸዋል።   ከሀገር አልፎ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሰረት ለቀጣናው እና ለአፍሪካ አህጉር ልምድና አቅም በማጋራት የአፍሪካ የዲጂታል ሽግግር መሪ እንድንሆን ያስችለናል። የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዟችን ስኬት የሚለካው በደረስንባቸው ቴክኖሎጂዎች ሳይሆን፣ ሕዝባችን እነዚህን ውጤቶች የራሱ አድርጎ ሲጠቀምባቸው እና ህይወቱ ሲለወጥ ነው። የቴክኖሎጂ አቅርቦታችንን ጥራት በመጠበቅ፣ የዳታ ደህንነታችንን በማረጋገጥ እና የዜጎቻችንን ዲጂታል ግንዛቤ በማሳደግ የያዝነውን አቅጣጫ በበለጠ ቁርጠኝነት እንቀጥላለን ብለዋል።
ስፖርት
በዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና የመክፈቻ ቀን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው የፍጻሜ ውድድሮች ይካሄዳሉ
Aug 5, 2026 141
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ከዛሬ ጀምሮ በአሜሪካ ኦሬጎን ይካሄዳል። ዛሬ ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ በሄይዋርድ ፊልድ ስታዲየም በሚጀመረው ሻምፒዮና ላይ ከ147 ሀገራት የተውጣጡ ከ1800 በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ። ኢትዮጵያም በሻምፒዮናው ላይ በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር (በሁለቱም ፆታዎች)፣ 3000 ሜትር መሰናክል (በሴቶች)፣ 400 ሜትር (በሴቶች) እንዲሁም በርምጃ ውድድር (በሁለቱም ፆታዎች) ትሳተፋለች። በውድድሩ ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ትናንት ኦሬጎን ደርሷል። በሻምፒዮናው መክፈቻ ቀን በሁለቱም ጾታዎች የ5000 ሜትር የፍጻሜ ውድድሮች ይካሄዳሉ። ንጋት 11 ሰዓት ከ53 ላይ በ5000 ሜትር ሴቶች አትሌት ሽቶ ጉሜ እና አትሌት እመቤት ጥላሁን ይወዳደራሉ። በአጠቃላይ 27 አትሌቶች በፍጻሜው ውድድር ላይ ይሳተፋሉ። ነገ ጠዋት 12 ሰዓት ከ20 ላይ በሚደረገው የወንዶች የ5000 ሜትር ፍጻሜ አትሌት ዳምጠው ከበደ እና አትሌት ማማሩ ጎዴ የሚሳተፉ ይሆናል። በተጨማሪም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው የማጣሪያ ውድድሮች ይከናወናሉ። ምሽት 4 ሰዓት ከ35 ላይ በሚካሄደው የ800 ሜትር ወንዶች የመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ነጋሄ እያሱ እና የሮሳን ግርማ ይሳተፋሉ። በአምስት ምድቦች ተከፍሎ በሚደረገው የማጣሪያ ውድድር ከየምድቡ ከአንድ እስከ አምስት የሚወጡ አትሌቶች ወደ ግማሽ ፍጻሜ ማጣሪያው በቀጥታ ያልፋሉ። ምርጥ ሰዓት ያስመዘገቡ ሁለት ተጨማሪ አትሌቶች ግማሽ ፍጻሜ ይገባሉ። ምሽት 5 ሰዓት ከ15 ላይ በሚደረገው የ800 ሜትር ሴቶች የመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ደራርቱ ሽብሩ እና ሀብታም ገበየሁ ኢትዮጵያን ወክለው ይወዳደራሉ። በአምስት ምድቦች በሚካሄደው የማጣሪያ ውድድር፣ ከእያንዳንዱ ምድብ ከአንደኛ እስከ አምስተኛ የሚወጡ አትሌቶች በቀጥታ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ያልፋሉ። ከዚህ በተጨማሪ፣ የተሻለ ሰዓት ያስመዘገቡ ሁለት ተጨማሪ አትሌቶች ግማሽ ፍጻሜውን ይቀላቀላሉ። 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። እ.አ.አ በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከዓለም ሁለተኛ በመሆን ማጠናቀቋ የሚታወስ ነው።
በበጀት ዓመቱ ህብረ-ብሔራዊ አብሮነትን ይበልጥ የሚያጠናክሩ ተግባራት ተከናውነዋል
Aug 5, 2026 115
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ህብረ-ብሔራዊ አብሮነትን ይበልጥ የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለፁ። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ፣ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት እና የቀጣይ ሶስት ዓመት የመካከለኛ ዘመን እና ዓመታዊ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ይገኛል።   የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በዚሁ ወቅት፤ በጉባኤው የባህል፣ የጥበባት እና ስፖርት ለሀገር ኢኮኖሚና ማህበራዊ ህይወት የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ በሳይንሳዊ መንገድ ለመደገፍና በቀጣይ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቀየስ የሚያስችል ውይይት እንደሚደረግበት ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ያነሱት ሚኒስትሯ፤ በበጀት ዓመቱ 47 የብሔር ብሔረሰቦች የዘመን መለወጫ በዓላት እና 5 ሀገር አቀፍ ክብረ በዓላት በተሳካ መንገድ መከበራቸውን ተናግረዋል። በነዚህ በዓላት ላይ ከ46 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በመሳተፍ ህብረ-ብሔራዊ አብሮነትን ይበልጥ ማጠናከሩን አስረድተዋል። በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ ባለፉት 28 ዓመታት ስራ ላይ የነበረው የስፖርት ፖሊሲ መሻሻሉን ገልጸው፤ ፖሊሲው ለኢኮኖሚው አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ታስቦ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በ2019 በጀት ዓመት ሙሉ ተቋማዊ ሪፎርም የማድረግና አሰራሮችን የማዘመን ስራዎች ልዩ ትኩረት ተሰጥቷቸው እንደሚከናወኑ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ ስፖርት ቱሪዝምን ማስፋፋት የሚያስችሉ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡   ባለሃብቶች ወደ ስፖርቱ ዘርፍ በብዛት እንዲገቡ የማበረታታት ስራ መሰራቱን ጠቅሰው 29 ዓለም አቀፍ የስፖርት ኮንፈረንሶችና ውድድሮች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውን አብራርተዋል።
ኒውካስትል ዩናይትድ ብሩኖ ጉማሬሽን ለአርሰናል ለመሸጥ ተስማማ
Aug 5, 2026 119
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የኒውካስትል ዩናይትዱ የአማካይ ተጫዋች ብሩኖ ጉማሬሽ ሻምፒዮኑ አርሰናልን ለመቀላቀል ከጫፍ ደርሷል። ጣልያናዊው የስፖርት ጋዜጠኛና በእግር ኳስ የዝውውር ዜናዎቹ የሚታወቀው ፋብሪዚዮ ሮማኖ ኒውካስትል ተጫዋቹን ለመሸጥ መስማማቱን ገልጿል።’ የጉማሬሽ የዝውውር ዋጋ 75 ሚሊዮን ፓውንድ መሆኑንም አመልክቷል። የ28 ዓመቱ ተጫዋች እ.አ.አ ጁላይ 2026 ላይ አርሰናልን ለመቀላቀል በግሉ ተስማምቶ እንደነበር የሚታወስ ነው። አሁን ላይ ሁለቱ ክለቦች በዝውውሩ ከስምምነት ላይ መድረሳቸው የተንዛዛውን የዝውውር ጉዳይ እንዲቋጭ አድርጎታል። ጉማሬሽ እ.አ.አ በ2022 ከሊዮን ወደ ኒውካስትል ዩናይትድ በመዘዋወር ሲጫወት ቆይቷል። ተጫዋቹ መድፈኞቹን መቀላቀሉ የቡድኑን የአማካይ ክፍል ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ይጠበቃል። ብሩኖ ጉማሬሽ ከክሪስቶስ ዞሊስ እና ኢላን ሜስሊዬር በመቀጠል አርሰናል በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት የሚቀላቀል ሶስተኛ ተጫዋች ይሆናል።
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ወደ አሜሪካ አመራ
Aug 3, 2026 408
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ)፦ በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት፣ ዩጂን ከተማ በሚካሄደው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ምሽቱን ወደ ውድድሩ ስፍራ አቅንቷል። ሻምፒዮናው በዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ታሪካዊ መድረክ በሆነው በሄይዋርድ ፊልድ ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን፣ ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ ወጣት አትሌቶች ይሳተፋሉ። ሻምፒዮናው ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። በዘንድሮው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር (በሁለቱም ፆታዎች)፣ 3000 ሜትር መሰናክል (በሴቶች)፣ 400 ሜትር (በሴቶች) እንዲሁም በርምጃ ውድድር (በሁለቱም ፆታዎች) ትሳተፋለች። የኢትዮጵያ አትሌቶች በሻምፒዮናው ላይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅታቸውን አድርገዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣ የፌዴሬሽኑ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አመንሲሳ ከበደ (ዶ/ር) እና የፌዴሬሽኑ የስልጠና፣ ጥናትና ምርምር ዳይሬክተር አሰፋ በቀለ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በመገኘት ልዑክ ቡድኑን መሸኘታቸውን የፌዴሬሽኑ መረጃ ያመለክታል። በዘንድሮው ሻምፒዮና ላይ ከ147 ሀገራት የተውጣጡ ከ1800 በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ። እ.አ.አ በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከዓለም ሁለተኛ በመሆን ማጠናቀቋ የሚታወስ ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የመደመር ፍሬ፡አረንጓዴዋ ኢትዮጵያ
Aug 5, 2026 164
በሙሴ መለሰ የመደመር እሳቤ ዋና መሠረቱ እውቀትን፣ጉልበትን፣ሀብትንና አቅምን አስተባብሮ ለአንድ የጋራ ዓላማ በጋራ ማቆምን ያመለክታል። ይህን የሃሳብ ልዕልና በተግባር ፈትሾ ተጨባጭ ውጤት የታየበት ላለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ነው። አረንጓዴ ዐሻራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን አግኝቷል። የአረንጓዴ ዐሻራ ትልቁ ማሳያ የህዝብ ህብረት የታየበት መሆኑ ነው። በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እድሜ፣ ጾታ እና ልዩነት ሳይበግራቸው በነቂስ በመውጣት በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል አኩሪ ታሪክ የሰሩበት ህዝባዊ ንቅናቄ የመደመርን አስተሳሰብ በተግባር ያረጋገጠ ነው። ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ ከተካሄደው የአንድ ጀምበር መርሃ ግብር እንደታየው፣መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያለ ምንም ክፍያ በሙሉ ፈቃደኝነት እና በዝናብ ውስጥ ውሎ ከ805 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ሰርቷል። በአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላው 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ተደምረው ለነገ ልጆቻቸው መሰረት ለመጣል ሲወስኑ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ለዓለም ህዝብ ያሳዩበት ህያው አብነት ነው። የመደመር እሳቤ በቃላት ሳይሆን በተጨባጭ ውጤት የሚለካ ነው፤ በዘንድሮው የችግኝ ተከላ ዘመቻ እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ቀሪው 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ደግሞ በቀጣይ ጊዜያት ይተከላል። በአንድ ወቅት ከ40 በመቶ በላይ የደን ሽፋን የነበራት ኢትዮጵያ ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሃብትና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት የደን ሽፋኗ ወደ 3 በመቶ ወርዶ ነበር። አረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ የደን ሽፋን ከነበረበት 17.2 ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በማሳደግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ችግኝ ተከላው ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ከምግብ ዋስትና እና ከሀገር ኢኮኖሚ ጋርም የተሳሰረ ነው። በፍራፍሬ እንደ አቮካዶ፣ማንጎ እና ቡና ባሉ ምርታማ ችግኞች ላይ በማተኮሩ የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባሻገር፣ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት የምትበለጽግ፣የማትለምን እና ለተቸገሩት የምትደርስ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል የዜጎችን ገቢ የማሳደግ ድርሻ አለው። ኢትዮጵያ ችግኞችን ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ያከናወነቻቸው የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስራዎች የመደመር እሳቤ ድንበር አቋርጦ ለአህጉራዊ ትስስር እና ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ የሚሆን ድንበር ተሻጋሪ እሴት እንዳለው ያሳያል። ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዋ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ ምክንያት ሆኗል። ይህም የኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት ዓለም አቀፍ እውቅናን አስገኝቷል። በአጠቃላይ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያን በቀና እሳቤ እና በትብብር በመቆም ተስፋን ለልጆቻቸው መዝራት እንደሚችሉ በተግባር፣በስራና በውጤት ያረጋገጡበት ትልቅ ሀገራዊ ኩራት ነው።
ኢትዮጵያ ንጹሕና አረንጓዴ ከተሞችን በመገንባት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተምሳሌት እየሆነች ነው
Aug 5, 2026 216
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ኢትዮጵያ ከተሞቿን አረንጓዴ፣ ንጹሕና ዘመናዊ የኑሮ ማዕከላት በማድረግ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ኦፊሰር ኸርነስት ቺ ቾ ገለጹ። ኦፊሰሩ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በአዲስ አበባ የአረንጓዴ ከተማ ፖሊሲዎች በተግባር መተግበራቸውና ሰፊ የመሠረተ ልማት ሥራዎች መከናወናቸው በከተማዋ ሁለንተናዊ ለውጥ እንዲመዘገብ አስችሏል። በተለይም በአዲስ አበባ ጎዳናዎች፣ ፓርኮችና የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች ላይ የታዩ ተጨባጭ ለውጦች ከተማዋን የተሻለ የኑሮ አካባቢ እንዲሆን እያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።   ከ10 ዓመታት በፊት ወደ አዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ መምጣታቸውን ያስታወሱት ኦፊሰሩ፣ የመንገድና የከተማ መሠረተ ልማቶች አሁን ከቀድሞው ጋር ሲነጻጸሩ እጅግ አስደናቂ ለውጥ እንዳሳዩ ገልጸዋል። ዘመናዊ ከተማ ማለት የተሻለ ደህንነት ያላቸው መንገዶች፣ አረንጓዴ የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎችና የተሟሉ መሠረተ ልማቶች ያሉባት ከተማ ናት ነው ብለዋል። በዚህም በአዲስ አበባ የፓርኮች፣ የሕፃናት መዝናኛ ስፍራዎችና ሌሎች የሕዝብ መገልገያዎች በስፋት መገንባታቸው የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት ስኬትም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያግዙ፣ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የማስፋፋት ጥረቶችም ወሳኝ የለውጥ አካል መሆናቸውን አክለዋል። ኢትዮጵያ ከተሞቿን አረንጓዴና ንጹሕ በማድረግ ለሌሎች ሀገራት አርዓያ መሆኗን ቀጥላለች ብለዋል።   በቱሪዝም ዘርፍም ኢትዮጵያ ተጨባጭ ለውጦችን በማስመዝገብ በአፍሪካ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑና ጥራታቸውን የጠበቁ በርካታ ሆቴሎች መገንባታቸው የዘርፉን ዕድገት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የተከናወኑ የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ሥራዎች ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አርዓያ ናቸው ያሉት ኦፊሰሩ፣ የኢትዮጵያ የሆቴሎች ጥራትና ብዛት በብዙ የአፍሪካ ከተሞች ከሚታየው እንደሚልቅ ገልጸዋል።   በሌላ በኩል የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ማግኘቱን ጠቅሰው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአፍሪካ ሞዴል የሆነ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ለውጤት ማብቃት ተችሏል
Aug 5, 2026 117
ደሴ ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦ በደቡብ ወሎ ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ለውጤት ማብቃት እንደተቻለ አርሶ አደሮች ተናገሩ፡፡ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 40 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ ችግኞችን የመትከል ስራ መጀመሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታውቋል።   በዞኑ ቃሉ ወረዳ የ021 ቀበሌ አርሶ አደር ደጉ መሀመድ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ መንግስት ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሰጠው ትኩረት ተጠቃሚ አድርጓቸዋል።   ቀደም ሲል ከተከሉት የማንጎ ችግኝ ፍሬ መስጠት በመጀመሩ ዘንድሮ 80 ሺህ ብር መሸጣቸውን ጠቁመው፣ ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ በተያዘው ክረምት ወቅትም 130 የማንጎ ችግኝ መትከላቸውን ተናግረዋል። የዚሁ ወረዳ የ019 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መሀመድ ሁሴን በበኩላቸው፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የመሬታችንን የአፈር ለምነት በመጠበቅ የሰብል ምርታማነታችንን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።   ባለፉት ዓመታት የተከልኳቸውን ችግኞች በአግባቡ በመንከባከብ ለውጤት ማብቃት ችለናል ያሉት አርሶ አደሩ፣ ዘንድሮ የተከልናቸውንም ተንከባክበን ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ እንሰራለን ብለዋል። ከተከሉዋቸው የባህር ዛፍ ችግኞች ለቤት መስሪያ የደረሰውን በመሸጥ በየዓመቱ እስከ 50 ሺህ ብር ገቢ እንደሚያገኙ የተናገሩት ደግሞ በደሴ ዙሪያ ወረዳ የ038 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ይመር አሊ ናቸው። ከዚህም እያገኙ ያለውን ጥቅም ለማሳደግ ከአንድ ሺህ 500 በላይ የባህር ዛፍ፣ አፕልና ሌሎችንም ችግኞች መትከላቸውን ገልጸዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አርሶ አደሩ በማሳውና በወል መሬቶች ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል ተጠቃሚ እያደረገው ነው።   በዞኑ ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች ምርታማነት እንዲጨምር፣ የደን ልማት እንዲጠናከርና የእንስሳት መኖን በቀላሉ ማግኘት እንዲቻል ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን አብራርተዋል፡፡ በዘንድሮው ክረምትም 40 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ችግኝ በመትከል የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በደቡብ ወሎ ዞን ባለፈው ዓመት ክረምት 33 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውንም ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የታየው የህዝብ አንድነት ለጋራ ዓላማ በመሰለፍ አዎንታዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ያረጋገጠ ነው - ምሁራን
Aug 5, 2026 169
ጅማ፤ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፡- በአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የታየው ህብረትና የህዝብ አንድነት ለጋራ ዓላማ በመሰለፍ ዘላቂና አዎንታዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጠ ነው ሲሉ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም ይፋ የተደረገ ሀገራዊ የደን ልማትና የአካባቢ ጥበቃ መርሃ ግብር ነው። መርሃ-ግብሩ በዋናነት የተወጠነው ፈጣን የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ፣ የመሬት መሸርሸርን ለመግታት፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የተመናመነውን የሀገሪቱን የደን ሽፋን ለማሳደግ ታስቦ ነው። በዚህም ባለፉት ዓመታት በመላ ሀገሪቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን የመርሃ ግብሩ አካል በሆነው በ"በአንድ ጀምበር" የችግኝ ተከላ ንቅናቄ ሕዝቡን በአንድ ላይ በማንቀሳቀስ መትከል ተችሏል። በዘንድሮው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ንቅናቄም 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘውን ግብ በኢትዮጵያውያን የተቀናጀ ትብብርና ንቁ ተሳትፎ ከዕቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል። ይህን አስመልክቶ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የጅማ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን፤ በአንድ ጀምበር የተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከተባበርን ሀገራችንን ማሳደግና መለወጥ እንደምንችል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ ግብርና እና እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ የተፈጥሮ ሀብት አያያዝ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ጥበቡ ዓለሙ (ዶ/ር) ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ችግኝ መትከሉ የኔነት ስሜትን ከመፍጠር ባለፈ ባህል እየሆነ እንደመጣ አመልክተዋል። የምናከናውናቸው የልማት ሥራዎች ኢትዮጵያን ወደተሻለ ደረጃ የሚያሻግሩና ለቀጣይ ትውልድ መሠረትን የሚጥሉ መሆናቸውን የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላው ስኬት አሳይቶናል ሲሉም አክለው ገልጸዋል። “የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ባለፉት ዓመታት ተዘርዝረው የማያልቁ ጠቀሜታዎችን አስገኝቷል" ያሉት ዶክተር ጥበቡ፤ ፕሮጀክቱ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር ከመቀየሩም በላይ ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። አክለውም ሴቶችና ሕፃናትን ጨምሮ ዘርና ቀለም ሳይለይ ዜጎችን በአንድነት ያስተሳሰረ እና ሕብረተሰቡ ችግኝ የመትከልን ጥቅም ይበልጥ እንዲገነዘብ ያደረገ ታላቅ ሀገራዊ ክስተት መሆኑን ተናግረዋል። መርሃ-ግብሩ የዓለም አቀፍ ተቋማትንና የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረት መሳቡን የጠቀሱት ምሁሩ፤ ይህም ኢትዮጵያውያን ከተባበሩ ተፅዕኖ ፈጣሪና አሸናፊ ሀገር መገንባት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ነው ብለዋል። "የአንድነትን ውጤት ማወቅ የሚፈልግ የዓድዋን ድል እና የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ማሰብ በቂው ነው" ያሉት ምሁሩ፤ ስንተባበር መገፋፋት እየቀነሰ እና መግባባት እየጎለበተ እንደሚሄድም ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው የግብርና እና እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ የተፈጥሮ ሀብት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ጌትነት ሰይድ በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደግና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ ትልቅና ተሻጋሪ ትርጉም ያለው መሆኑን አስረድተዋል። "የአየር ንብረት ለውጥ ዓለምን እያስጨነቀ ባለበት በዚህ ወቅት፣ አንድነታችን ከሀገር አልፎ ለዓለም ችግር የመፍትሔ አካል እየሆነ ነው" ሲሉም አክለው ገልጸዋል። በተለይም በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዜጎች ያለ ምንም ልዩነት በየዓመቱ በአንድነት አሻራቸውን ማሳረፋቸው፤ ለሰላማችን፣ ለእድገታችን እና ድህነትን ለማጥፋት ተኪ የሌለው ሚናን ይጫወታል ብለዋል።  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 165
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 295
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 621
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1075
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
ያቀደችውን በተግባር የምታሳካ ታላቅ ሀገር
Aug 3, 2026 569
የአንድ ሀገር ታላቅነት ከሚለካባቸው ጉዳዮች አንዱ የተያዙ ሀገራዊ እቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም ዋነኛው ነው። ኢትዮጵያም በዛሬው እለት በአንድ ጀምበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አዲስ ታሪካዊ ስኬት፣ ሀገሪቱ ያቀደችውን በተግባር ማሳየት የምትችልና ትልልቅ ህልሞችን የመተርጎም አቅም ያላት ታላቅ ሀገር መሆኗን ለመላው ዓለም በተግባር ያስመሰከረ ነው። ይህ በአንድ ጀምበር የተከናወነ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በርካታ ጥልቅ ትርጉሞችን የያዘ ነው፡ በአንድ ጀንበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ግዙፍ የሎጂስቲክስ፣ የዝግጅትና የህዝብ ንቅናቄ ስራን ይጠይቃል።   ይህ ስኬት ሀገሪቱ ማንኛውንም ታላቅ አገራዊ እቅድ አቅዳ እስከ መጨረሻው የትግበራ ምዕራፍ ድረስ በብቃት የመምራትና የማስተባበር ተቋማዊና ህዝባዊ አቅም እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ዕድሜ፣ ጾታ፣ ወይም ልዩነት ሳይለያያቸው በአንድ ቀን ለተመሳሳይ አገራዊ ዓላማ መቆማቸው፣ ኢትዮጵያውያን ለጋራ እድገታቸውና ለሀገራቸው የወደፊት ተስፋ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትና አንድነት አሳይቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት ዋና ስጋት በሆነበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ እርምጃ ለችግሩ መፍትሔ በመስጠት ረገድ የዓለም አቀፍ መሪነቷን ያስመሰከረችበት አጋጣሚም ጭምር ነው። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የገጠሟትን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፈተናዎች ተሻግራ፣ አቅሟን አስተባብራ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ለዜጎቿም ሆነ ለውጭው ዓለም የሰጠችው ትልቅ የራስ መተማመንና የተስፋ መልእክት ነው። በአጠቃላይ፣ በአንድ ጀምበር የተከናወነው ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ አርቆ የማሰብና የማቀድ ችሎታዋን ብቻ ሳይሆን፣ ያቀደችውንም በአንድነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት በማውረድ በተግባር የምታሳይ ታላቅ ሀገር መሆኗን በግልጽ ያረጋገጠ አኩሪ ተግባር ነው።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ ትንሳኤ ብስራት!!
Aug 2, 2026 403
በሐዊ አጫሉ መግቢያ፡- የኢንዱስትሪ ዘርፍ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬን ከሚወስኑ ዋነኛ የብልፅግና ማረጋገጫ ምሰሶዎች መካከል በግምባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ዘርፉ ምርትን ከማሳደግ ባሻገር የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የሀገር ውስጥ ምርታማነትን የሚያፋጥን የልማት ሞተር ነው። ኢትዮጵያም ከግብርና መሠረት የተነሳ ኢኮኖሚዋን ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ሁሉን አቀፍ የምርት ሥርዓት ለማሸጋገር ከምታደርገው ጥረት መካከል ኢንዱስትሪውን በቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶነት በማካተት እየሰራችበት ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ አምስት ዐበይት የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት ምሰሶዎች ተመሥርቶ እየተመራ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥ ኢንዱስትሪው የምርት አቅምን በማሳደግ የግብርና ምርቶችን ወደ ተጨማሪ እሴት በመቀየርና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ እያስገኘ ነው። ይህንን ሽግግር እውን ለማድረግ የምርት አቅምን ማሳደግ፣ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር፣ የአቅርቦት ሰንሰለትን ማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና የሰው ኃይል ልማት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ የቀድሞ ገጽታ፤ ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ለውጥ መንገድ!! በቀደሙት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለያዩ ዕድሎችንና ፈተናዎችን በማስተናገድ በርካታ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል። ሀገሪቱን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር በተደረጉ ጥረቶች የተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተገንብተዋል። እነዚህ ፓርኮችም በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የተሞከረበት ወሳኝ ምዕራፍ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ ይህ ጉዞ በበቂ መሠረተ ልማት፣ በተሟላ የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና በተቀናጀ የምርት ሰንሰለት እጥረት ምክንያት በበርካታ ፈተናዎች ለመውደቅ ተገዶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ውስንነት፣ ዕውቅትና ክህሎትን የተሰላበሰ የሰው ኃይል አለመኖር፣ የፋይናንስ እጥረት፣ ውስብስብና አስቸጋሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትና የገበያ ትስስር እጥረት የዘርፉን እድገት ገድበው የነበሩ ሁነኛ ተግዳሮቶች ናቸው። ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ምርታማነት፤ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የለውጥ ፍኖት!! ባለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ ዘርፉ የተስተዋሉ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታትና የሀገሪቱን የማምረት አቅም ለማሳደግ አዳዲስ የለውጥ አቅጣጫዎች ተነድፈው ተተግበረዋል። በተለይም ኢንዱስትሪን ከተለመደው የምርት ሥርዓት በማሻገር ወደ ተወዳዳሪ ዘመናዊና ውጤታማ የማምረቻ ማዕከል ለመቀየር የተለያዩ የፖሊሲማሻሻያዎች ተደርገዋል። የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ፣ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን፣ የሰው ኃይል አቅምን ማሳደግና የግብርና-ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር በዘርፉ የተወሰዱ ሁነኛ የለውጥ እርምጃዎች ናቸው። በዚህም የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት በማጎልበት ከሀገር ውስጥ ገበያ እስከ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ድረስ ውጤት እያስገኘ ነው። የግል ባለሃብቱ ሚና፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሞተር!! የኢንዱስትሪ ልማት በመንግሥት ጥረት ብቻ የሚሳካ አይደለም። የግል ዘርፉ በካፒታል፣ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂና በአስተዳደር ብቃት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ለዘርፉ ዕድገት የማይተካ ሚና አለው። በዚህ ረገድ የግል ባለሃብቱ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዋና አጋር እንዲሆን የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተሻሽለው እየተሰራባቸው ይገኛል። ይህም የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት በማሻሻል፣ የንግድ ሥራ ሂደቶችን በማቀላጠፍ፣ የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋትና የምርት አቅምን በማሳደግ የግሉን ዘርፉ የምርታማነት አቅም እያጎለበተ ነው። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትንሳኤ ብስራት!! በሀገራችን የኢኮኖሚ አቅጣጫ ውስጥ የምርትና አገልግሎት አሰጣጥን በማቀናጀት አዲስ ምዕራፍ ከከፈቱ ዐበይት ሀገራዊ መርሃ-ግብሮች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተጠቃሽ ነው። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማምረት ባህልን በማሳደግ ዘርፉ ወደ አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚሸጋገርበት ሁነኛ ዕድልን ፈጥሯል። ንቅናቄው የማምረት አቅምን በማሳደግ ሥራ ያቆሙ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ መመለስ፣ የአምራቾችን ችግሮች በፍጥነት መፍታትና አዳዲስ ባለሃብቶችን ወደ ዘርፉ በመሳብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤ እያበረከተም ይገኛል። በዚህ ሂደት በፋይናንስ፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በውጭ ምንዛሬና በተቋማዊ ቅንጅት ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎች የአምራች ዘርፉን የምርታማነት አቅም በማጎልበት ጉልህ ሚና ተጫውቷል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲያንሰራራ በማድረግ የምርታማነት አብዮት እንዲቀጣጠል እያደረገ ይገኛል። የንቅናቄው ዋና ዓላማ በአምራች ዘርፉ የነበሩ ማነቆዎችን በመፍታት የኢትዮጵያን የማምረት አቅም ማሳደግ ነው። ይህም ሥራ ያቆሙ ወይም በአቅማቸው ልክ ያልሠሩ ፋብሪካዎችን ወደ ሙሉ ምርት በመመለስ የአምራቾችን ችግር በተቀናጀ መንገድ መፍታት፣ የፋይናንስና የግብዓት ተደራሽነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጓል። በዚህ ሂደት የማምረቻ ዘርፉ በአዲስ የሥራ ባህል፣ በተቋማዊ ቅንጅትና በፈጣን ውሳኔ አሰጣጥ እየተመራ መሆኑ የለውጡን ፍጥነት እያሳደገው ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ተደራሽነትን ማሻሻልና የምርት ጥራትን ማረጋገጥ የኢንዱስትሪው ትንሳኤ ዋና ማሳያዎች ናቸው። ለአብነትም፡- የፋይናንስ አቅምና የብድር አቅርቦት ማሻሻል፡- የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ እንቅፋት የሆነውን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ በተደረገው ርብርብ፣ የብድር አቅም ቀደም ሲል ከነበረበት 40 ቢሊዮን ብር ወደ 115 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ለአምራቾች ሰፊ የካፒታል አቅም መፍጠር ተችሏል። የውጭ ምንዛሬ ግኝትና የግብዓት ድጋፍ ማደግ፡- ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ይቀርብ የነበረው የውጭ ምንዛሬ መጠን አሁን ላይ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንዲደርስ ተደርጓል። ይህም ፋብሪካዎች ከአቅማቸው በታች እንዲሠሩ ያስገድድ የነበረውን የምርት ውስንነት በከፍተኛ ደረጃ አቃሎታል። የምርት ዕድገት፣ ተኪ ምርትና የኤክስፖርት አፈጻጸም፡- ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ ከነበረበት 348 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5.9 ቢሊዮን ዶላር በማደግ ግዙፍ ሀገራዊ ድል ተመዝግቧል። እንዲሁም በኤክስፖርት ገበያ የሚገኘው ገቢ ከ385 ሚሊዮን ዶላር ወደ 607 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ማለት ችሏል። ተቋማዊ ቅንጅትና አዲስ የሥራ ባህል ማዳበር፡- በክልሎችና በፌዴራል ተቋማት መካከል የነበረውን የቢሮክራሲ ጫና በመቀነስ ፈጣን ውሳኔዎች እንዲሰጡ መደረጉ፤ እንዲሁም ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርትን በኩራት የመጠቀም እና የሀገር ፍቅር ስሜትን ከአምራችነት ጋር የማስተሳሰር ትልቅ ማህበራዊ ንቃተ-ህሊና መገንባት ተችሏል። የወደፊት ተስፋ፤ ኢትዮጵያ አዲሲቷ አፍሪካዊት የኢንዱስትሪ ምርታማነት ተምሳሌት ሀገር!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ በቀጣይ ዓመታት ከተለመደው ማምረት ወደ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ሥርዓት እንዲሸጋገር ይጠበቃል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሜሽን፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና የፈጠራ ሥርዓቶችን ወደ ማምረቻ ዘርፉ ማስገባት የወደፊቱ ትኩረት ይሆናል። በተመሳሳይም ጠንካራ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስር፣ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት፣ ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአህጉራዊ ገበያ ተደራሽነት የሀገሪቱ ቀጣይ የኢንዱስትሪ ግቦች ናቸው። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) የሚፈጥረውን ሰፊ የገበያ ዕድል በመጠቀም ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችል መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ማጠቃለያ፡- ማምረት፤ የኢትዮጵያ የብልፅግና ቁልፍ መሳሪያ!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ተጨማሪ እሴት ያለው ምርት አቅራቢነት በማምራት እመርታዊ ውጤቶችን እያስገኘ ነው። የኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ማለት ፋብሪካዎችን ብቻ ማስፋፋት ሳይሆን የሀገርን ምርታማነት፣ የወጣቶችን ዕድል፣ የኢኮኖሚ ነፃነትንና የልማት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን የዛሬ ልማት ብቻ ሳይሆን የነገውን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚገነባ ሀገራዊ ራዕይ ነው።  
የክልሎች ቅኝት - በወፍ በረር
Aug 2, 2026 290
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ) የክልሎች ቅኝት - በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግብርናውን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ድርሻ አበርክተዋል። በክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5 ዓመት 3ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የተጠናቀቀውን በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም በክልሉ የግብርናውን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱን አንስተዋል። የሜካናይዜሽን እርሻም ተግባራዊ በመደረጉ ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱንም ጠቅሰዋል። ከማዕድን ዘርፍም በበጀት ዓመቱ ከ 8 ሺህ 900 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል። ኦሮሚያ ክልል በኦሮሚያ ክልል የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ግልጽ እና ተጠያቂነት ያለበት በማድረግ የሙስና እና የብልሹ አሰራር ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ሪፎርም እየተተገበረ ይገኛል። ለዚህም የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራ ይፋ የማድረጊያ መርሃ ግብር ''የአገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ለሁለንተናዊ ብልጽግና'' በሚል መሪ ሀሳብ በቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል።   የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ የመንግስትን አገልግሎት አሰጣጥን የተሳለጠ ለማድረግ የሚያስችል እስከ ቀበሌ የደረሰ አሰራር መዘርጋቱን በወቅቱ አንስተዋል። አልግሎቶችን በዲጂታል ስርዓት በመደገፍ የህዝቡን እንግልት፣ ጊዜና ወጪ በመቆጠብ ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል። ይህም በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ሲዳማ ክልል የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ የ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት ንቅናቄ መድረክ ላይ በመገኘት ባደረጉት ንግግር በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ሥራ ምቹ ማድረግና በግብአት ለማሟላት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።   ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ስራ ምቹ በማድረግ በትምህርት ጥራት ላይ አዎንታዊ ለውጥ እንዲታይ መደረጉንም አስረድተዋል። ጋምቤላ ክልል ‎የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ''ተስፋን እንትከል'' በሚል መሪ ሀሳብ የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማጃንግ ዞን በመንገሺ ወረዳ ያስጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። በክልሉ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን ለማረጋገጥ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራዎች በህዝብ ተሳትፎ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል ።   ባለፉት ዓመታት የተከናወኑት የአረንጓዴ አሻራ ልማት የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ ከማድረጋቸው ባለፈ የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻሉንም ርዕሰ መስተዳድሯ ገልፀዋል። ‎አማራ ክልል በአማራ ክልል የግብርናን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለኢንዱስትሪዎች ግብአት ማምረት ተችሏል። የዚሁ አካል የሆነው በክልሉ በሰሜን ሸዋ ዞን በሞረትና ጅሩ ወረዳ 837 አርሶ አደሮች በማህበር በመደረጃት “የጅሩ-አግሮ ቢዝነስ“ ኩባንያን መስርተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት ኩባንያው የአርሶ አደሮችን ምርት በማቀነባበር ለገበያ የሚያቀርብ ነው። የአግሮ-ቢዝነስ ኩባንያውም ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አርሶ አደሩ ከጥሬ ግብአት አቅራቢነት ወደ አምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስተርነት በማደግ ላይ መሆኑን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል። ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳዳር ዙሪያ ጨታ ቀበሌ የተገነባውን የባቾ ገጠር ሞዴል መንደር መርቀው ለነዋሪዎች አስረክበዋል። በወቅቱም የሞዴል የገጠር መንደሩ መገንባት የሌማት ትሩፋት ስራዎችን ውጤታማ በማድረግ የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ አቅም ለማሳደግ ብሎም ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል።   በሌላ በኩል በክልሉ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ገንብቶ በማጠናቀቅ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በተለይም የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በመገንባት የወረዳና ቀበሌዎች ማህበራዊ ትስስር እንዲጠናከርና የግብይት ሰንሰለትም እንዲቀላጠፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። ለአብነትም በክልሉ ኮንታ ዞን በአመያ ዙሪያ ወረዳ በኡማ ወንዝ ላይ የተገነባው ድልድይ የአካባቢውን ነዋሪዎች የዘመናት ችግር ያቃለለና ለመሰረተ ልማት ጥያቄያቸው ምላሽ የሰጠ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ በክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ማስተዋወቂያ መድረክ ላይ በመገኘት ንግግር አድርገዋል።   በመልእክታቸውም በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት እየተደረገ ባለው ጥረት ውጤት እየተገኘ ስለመሆኑ ተናግረዋል። በ2019 በጀት ዓመትም በክልሉ በተደራጀ ህዝባዊ ንቅናቄ 48 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ግብር ለመሰብሰብ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል። ለዚህም በህግና የአሠራር ስርአት በመታገዝ የገቢ አቅምን በማስፋት የክልሉን ዕድገት ዘላቂነት በማረጋገጥ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቀዋል። በተመሳሳይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር ጉባኤ በአርባ ምንጭ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት እየተደረገ ባለው ጥረት ውጤት እየተገኘ ነው ብለዋል ። በ2019 በጀት አመትም የክልሉን የገቢ አቅም ለይቶ በተደራጀ ህዝባዊ ንቅናቄ የግብር እቅድን ለማሳካት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በዚህም በበጀት አመቱ 48 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል። ገቢውን ለማሳካትም የህግና የአሠራር ስርአት በመዘርጋት የክልሉ ዕድገት በዘላቂነት በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቀዋል። አፋር ክልል በአፋር ክልል የእንሰሳትና ዓሳ ሀብትን በማልማት ለወጣቶች የስራ እድልን ለማስፋት የተሰሩ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የክልሉ የእንሰሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ ኀላፊ አቶ ኢብራሂም መሐመድ ገልጸዋል። ለዚህም ስምንት የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሐይቆች ላይ ወጣቶችን አደራጅቶ ወደ አሳ ልማት ስራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል። ለአብነትም በአፋምቦ ሐይቅ ላይ 200 ወጣቶች በዓሳ ሀብት ልማት ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ የሚሆኑበት አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል። በዓሳ ሀብት ልማቱ ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች እንዳሉት የአሳ ሀብትን አልምተው ተጠቃሚ ለመሆን በማህበር ተደራጅተው በመስራት ላይ ናቸው። ስራውንም ለማሳካት ክልሉ እያደረገ ያለው የሙያ ስልጠናና ድጋፍ የማይተካ ድርሻ አለው ብለዋል። ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል "ሁሉ አቀፍ እመርታ ፣ ለሁለንተናዊ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራ አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የከፍተኛ አመራሮች የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።   ርዕስ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል። የህዝቦችን አብሮነት በማጠናከር ክልሉን የህብረ ብሄራዊነት ተምሳሌት ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል። በበጀት ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችን ማጠናከርና የተስተዋሉ ጉድለቶችን በማረም ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ የመድረኩ ዋና ዓላማ ስለመሆኑም ገልጸዋል። ሐረሪ ክልል የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሃላፊ ሮዛ ኡመር እንደገለፀት፤ በክልሉ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ስራ በገጠር ወረዳዎች የመስኖ ልማት በስፋት ተከናውነዋል። ተግባሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ የ2018 የግብርና ልማት እቅድ አፈጻጸምና የ2019 የግብርና ልማት መሪ እቅድ ላይ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።   በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የእንስሳት ተዋጽኦና የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ትልቅ እመርታ የተገኘበት ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባሻገር የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ ተወጥቷል ብለዋል። ሶማሌ ክልል የሶማሌ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባዔውን ሲያካሂድ ርእሰ መስተዳድሩ ሙስጠፌ ሙሀመድ፤ የተጠናቀቀውን በጀት ዓመት ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም በክልሉ የሰላምና የልማት እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ስራዎችና የመጡ ውጤቶችን አብራርተዋል።   የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው፤ የፍትህ አካላትን አቅም ለመገንባት በተደረገ ጥረት የፍትህ ሂደቱ የተሳለጠ እንዲሆን መቻሉንም አንስተዋል። በክልሉ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በድህነት ቅንሳ፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እንዲሁም በተፈጥሮና በሰው ሠራሽ የሚመጡ አደጋዎች ቅነሳም ከፍተኛ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።      
ከሀገር አቀፍ ንቅናቄ እስከ ዓለም አቀፍ እውቅና፦የአረንጓዴ አሻራ ውጤታማ አበርክቶ
Jul 30, 2026 619
በታዋቂ ዓለም አቀፍ የሳይንስ መጽሔቶች ላይ የታተሙ ተከታታይ ጥናቶች የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር በደን መልሶ ማልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተዕፅኖን በመከላከል ፣ የካርበን ክምችት በማሳደግ እና በማህበረሰብ ተሳትፎ ረገድ ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ መሆኑን አረጋገጡ። የጥናቱ ግኝቶች ከስምንት ዓመታት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)አነሳሽነት የተጀመረው የአረጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር፣ በአፍሪካ ግዙፍ እና እጅግ ውጤታማ ወደሆነ የመሬት ገጽታ መልሶ ማልማት ፕሮግራም ማደጉን የሚያሳይ ጠንካራ ሳይንሳዊ ማስረጃ አቅርበዋል። ኔቸር ፖርትፎሊዮ (Nature Portfolio)፣ ኤልሴቪየር (Elsevier) እና ስፕሪንገር (Springer)ን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባላቸው አሳታሚዎች እ.ኤ.አ. በ2026 የወጡ አምስት ጥናቶች፤ የሳተላይት ምስሎችን፣ የመስክ የዳሰሳ ጥናቶችን፣ የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂዎችን እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም የመርሐ-ግብሩን አካባቢያዊ ፋይዳ ገምግመዋል። ከፍተኛ የችግኝ ጽድቀት ምጣኔ - የውጤታማ መልሶ ማልማት ማሳያ በኤልሴቪየር 'ትሪስ፣ ፎረስስ ኤንድ ፒፕል' (Trees, Forests and People) መጽሔት ላይ የታተመ ጥናት (አሰፋ እና ሌሎች፣ 2026) እንዳመለከተው፣ በደቡብ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የተተከሉ የዛፍ ችግኞች 80 በመቶ የሚገመት የጽድቀት ምጣኔ አስመዝግበዋል፤ ይህም ከሌሎች በርካታ ሰፊ የደን ልማት ፕሮግራሞች ልቆ የተገኘ ነው። ተመራማሪዎቹ ለዚህ ስኬት በዋነኛነት የጠቀሷቸው የተሻሻሉ የመልሶ ማልማት ልምዶችን ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል በዋናው የክረምት ወቅት መትከል፣ ጥንቃቄ የተሞላበት የቦታ ምርጫ፣ እንዲሁም በቴክኒክ ስልጠና የታገዘ ጠንካራ ማህበረሰብ አቀፍ እንክብካቤ ይገኙበታል። የጥናቱ መሪ ዶ/ር ታደሰ አሰፋ እንደገለጹት፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ከሳይንሳዊ የደን አያያዝ ጋር ማቀናጀት አዳዲስ ተከላ የተካሄደባቸው አካባቢዎች ጊዜያዊ የችግኝ መትከያ ቦታዎች ብቻ ሆነው ከመቅረት ይልቅ ዘላቂ ወደሆነ ደንነት እንዲያድጉ አስችሏል።   የማህበረሰብ ተሳትፎ ለስኬቱ ሞተር ነው በስፕሪንገር 'ዲስከቨር ኢንቫይሮመንት' (Discover Environment) ላይ የታተመ ሌላ ጥናት ደግሞ ሰፊው የማህበረሰብ ተሳትፎ የመርሐ-ግብሩ ታላቅ ጥንካሬ መሆኑን አመልክቷል። የጥናቱ መሪ ዶ/ር አብዱረዛቅ ሀጂ እንዳስገነዘቡት፣ እያደገ የመጣው የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ እና በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ የህዝብ ተነሳሽነት፣ አባወራዎች ችግኝ መትከልን የአካባቢን የመቋቋም አቅም ለመገንባት፣ ለዘላቂ ግብርና እና ለወደፊት የኑሮ መሰረት እንደተደረገ ኢንቨስትመንት እንዲመለከቱት አድርጓል። የህዝብ ተሳትፎ የመርሐ-ግብሩ የረጅም ጊዜ ስኬት የማዕዘን ድንጋይ መሆኑን ጥናቱ በማጠቃለያው አስቀምጧል። የደን ሽፋን ማደግ የአካባቢን አየር ንብረት ያሻሽላል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ቡኖ በደሌ ዞን የተካሄደ ጥናት በስድስት ዓመታት ውስጥ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን፣ ማለትምከ27.64 በመቶ ወደ 38.24 በመቶ ከፍ ማለቱን አስመዝግቧል። ጥናቱ የመሬት ገጽ የሙቀት መጠን እስከ 1.16 ዲግሪ ሴልሺየስ መቀነሱን ያረጋገጠ ሲሆን፣ ይህም የደን ሽፋን መስፋፋትየአካባቢውን አየር ንብረት እያሻሻለ እና የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅምን እያጠናከረ መሆኑንያሳያል። እነዚህ ለውጦች የስነ-ምህዳር አገልግሎቶችን እንደሚያሳድጉ እና የግብርና ምርታማነትን እንደሚደግፉ ይጠበቃል ሲሉ ተመራማሪዎቹተናግረዋል። ጥናቶች ከፍተኛ የካርበን ክምችት አቅም መኖሩን አጉልተዋልበኔቸር ፖርትፎሊዮ (Nature Portfolio) ሥር በ'ሳይንቲፊክ ሪፖርትስ' መጽሔት ላይየወጣ ሌላ ጥናት፣ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የዛፍ ዝርያዎች እና የግብርና-ደን ሥርዓቶች ከፍተኛ መጠንያለው የካርበን ዳይኦክሳይድ ክምችት የመያዝ አቅም እንዳላቸው አረጋግጧል። አንዳንድ መልመው ያገገሙ መሬቶች በሄክታር ወደ 500 ሜጋግራም የሚጠጋ የካርበን ዳይኦክሳይድ መጠን የያዙ መሆናቸው የተረጋገጠሲሆን፣ ይህም መርሐ-ግብሩ የአየር ንብረት ለውጥን በማቃለል ረገድ ያለውን ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያሳያል። የደን መልሶ ማልማት ስራውን ማስፋፋት የኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት እርምጃ ተሳትፎ የበለጠ እንደሚያጠናክርናበማደግ ላይ ባለው የዓለም አቀፍ የካርበን ገበያ ላይ ዕድሎችን እንደሚፈጥር ተመራማሪዎቹ ገልጸዋል።   አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የደን ዕድገቱ እንደሚቀጥል ተንብዮአል ማሽን ለርኒንግ፣ የሳተላይት ምስሎች እና የጂኦስፓሻል ትንታኔዎችን በመጠቀም በስፕሪንገር 'ኢንቫይሮመንታል ሞኒተሪንግ ኤንድአሴስመንት' (Environmental Monitoring and Assessment) መጽሔት ላይ የታተመ ሌላ ጥናት እንዳመላከተው፣አሁን ያለው የመልሶ ማልማት ጥረት ከተቀጠለ የኢትዮጵያ የደን ሽፋን ቢያንስ እስከ 2035 ድረስ መስፋፋቱን እንደሚቀጥልተንብዮአል። በመሬት ገጽታ መልሶ ማልማት ላይ የሚደረገው ተከታታይ ኢንቨስትመንት የደን ሽፋንን የበለጠ እንደሚያሳድግ፣ የካርበን ክምችትንእንደሚያጠናክር እንዲሁም የኢትዮጵያን የአየር ንብረት እና የዘላቂ ልማት ግቦችን እንደሚደግፍ ጥናቱ ያሳያል።   ዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ እውቅና በአጠቃላይ ሲታይ፣ አምስቱ ገለልተኛ ጥናቶች የኢትዮጵያን አረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ሁለንተናዊ ሳይንሳዊ ግምገማ በማቅረብ፤በደን መልሶ ማልማት፣ በካርበን ክምችት፣ በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም እና በህዝብ ተሳትፎ ረገድ የሚለኩና ተጨባጭ ውጤቶችንማምጣቱን ደምድመዋል። እነዚህ ግኝቶች የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የሰፊ ሥነ-ምህዳር መልሶ ማልማት ቀዳሚ ሞዴል በማድረግ ያስቀመጡትሲሆን፤ ዘላቂ የፖለቲካ ቁርጠኝነት፣ ሳይንሳዊ ዕቅድ እና አገር አቀፍ የህዝብ ንቅናቄ እንዴት ተጨባጭ የአካባቢ ጥበቃ ውጤቶችንማምጣት እንደሚችሉና፣ ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ እና የመሬት መራቆትን ለመከላከል ለሚደረጉ ጥረቶች ከፍተኛ አስተዋጽዖእንደሚያበረክቱ በጉልህ አሳይተዋል።
ትንታኔዎች
የመደመር ፍሬ፡አረንጓዴዋ ኢትዮጵያ
Aug 5, 2026 164
በሙሴ መለሰ የመደመር እሳቤ ዋና መሠረቱ እውቀትን፣ጉልበትን፣ሀብትንና አቅምን አስተባብሮ ለአንድ የጋራ ዓላማ በጋራ ማቆምን ያመለክታል። ይህን የሃሳብ ልዕልና በተግባር ፈትሾ ተጨባጭ ውጤት የታየበት ላለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ነው። አረንጓዴ ዐሻራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን አግኝቷል። የአረንጓዴ ዐሻራ ትልቁ ማሳያ የህዝብ ህብረት የታየበት መሆኑ ነው። በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እድሜ፣ ጾታ እና ልዩነት ሳይበግራቸው በነቂስ በመውጣት በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል አኩሪ ታሪክ የሰሩበት ህዝባዊ ንቅናቄ የመደመርን አስተሳሰብ በተግባር ያረጋገጠ ነው። ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ ከተካሄደው የአንድ ጀምበር መርሃ ግብር እንደታየው፣መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያለ ምንም ክፍያ በሙሉ ፈቃደኝነት እና በዝናብ ውስጥ ውሎ ከ805 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ሰርቷል። በአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላው 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ተደምረው ለነገ ልጆቻቸው መሰረት ለመጣል ሲወስኑ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ለዓለም ህዝብ ያሳዩበት ህያው አብነት ነው። የመደመር እሳቤ በቃላት ሳይሆን በተጨባጭ ውጤት የሚለካ ነው፤ በዘንድሮው የችግኝ ተከላ ዘመቻ እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ቀሪው 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ደግሞ በቀጣይ ጊዜያት ይተከላል። በአንድ ወቅት ከ40 በመቶ በላይ የደን ሽፋን የነበራት ኢትዮጵያ ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሃብትና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት የደን ሽፋኗ ወደ 3 በመቶ ወርዶ ነበር። አረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ የደን ሽፋን ከነበረበት 17.2 ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በማሳደግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ችግኝ ተከላው ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ከምግብ ዋስትና እና ከሀገር ኢኮኖሚ ጋርም የተሳሰረ ነው። በፍራፍሬ እንደ አቮካዶ፣ማንጎ እና ቡና ባሉ ምርታማ ችግኞች ላይ በማተኮሩ የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባሻገር፣ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት የምትበለጽግ፣የማትለምን እና ለተቸገሩት የምትደርስ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል የዜጎችን ገቢ የማሳደግ ድርሻ አለው። ኢትዮጵያ ችግኞችን ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ያከናወነቻቸው የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስራዎች የመደመር እሳቤ ድንበር አቋርጦ ለአህጉራዊ ትስስር እና ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ የሚሆን ድንበር ተሻጋሪ እሴት እንዳለው ያሳያል። ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዋ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ ምክንያት ሆኗል። ይህም የኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት ዓለም አቀፍ እውቅናን አስገኝቷል። በአጠቃላይ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያን በቀና እሳቤ እና በትብብር በመቆም ተስፋን ለልጆቻቸው መዝራት እንደሚችሉ በተግባር፣በስራና በውጤት ያረጋገጡበት ትልቅ ሀገራዊ ኩራት ነው።
በተቃርኖ የተሞላው ሕገ ወጡ ሕወሓት የጥፋት ጉዞ
Jul 30, 2026 606
የሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የፖለቲካ ጉዞ በበርካታ መሠረታዊ ተቃርኖዎችና የፖለቲካ ስህተቶች የተሞላ ነው። ቡድኑ በትግል ጊዜም ይሁን ሀገርን በመምራት ባደረገው የፖለቲካ ተሳትፎ ታሪክ ይቅር የማይላቸው ስህተቶችን ፈጽሟል። ከሁሉም በላይ የትግራይን ሕዝብ ለዘመን ተሻጋሪ መከራና ስቃይ ዳርጓል። የወጣቶችን ተስፋ እና ሕልም አጨልሟል። የሕገ ወጡ ቡድን በተቃርኖ የተሞላ ጉዞ በጨረፍታ እንመልከት። ተቃርኖ አንድ፦ የሀገር ገዥነት እና የነጻ አውጪነት መንፈስ ሕገ ወጡ ሕወሓት ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ግንባር ፈጥሮ ሀገር በመራበት ዘመንም ጉዞው በተቃርኖ የተሞላ ነበር። በዚህ የሥልጣን ዘመኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ከአንድነት ይልቅ ልዩነትን፤ ከኅብረት ይልቅ መነጠልን ሥር እንዲሰድ አድርጓል። በስም ደረጃ ሕብረ ብሔራዊ የፌዴራል ሥርዓት እንደሚያራምድ ቢናገርም ለኢትዮጵያውያን የተለያየ የዳቦ ስም በመስጠት እርስ በእርስ እንዲጠራጠሩ በማድረግ የጥላቻ ፖለቲካን አንግሷል። የሕግ የበላይነት እና የሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት በአንዱ ቡድን ላይ የማይተገበር ሌላው ላይ ግን ተግባራዊ እንዲሆን አድርጓል። ከቡድኑ ጋር የጥቅም ትስስር ያላቸው ቡድኖች ለሕግ የማይገዙ፣ ከኮንትሮባንድ እስከ ዓለም አቀፍ ወንጀሎች ውስጥ የሚሳተፉ ነበሩ። ሌላው ጽንፈኛ፣ አክራሪ እና ተስፋፊ ተደርጎ በሽብር እየተወነጀለ በየማረሚያ ቤቱ እንዲንገላታ ተደርጓል። በጥቅሉ ሕገ-መንግሥት እና የፌዴራል ሥርዓትን ለራሱ በሚያመች መልኩ ሲጠቀምበት ቆይቷል። ከዚህም ባለፈ ሕገ ወጡ ቡድን ሀገርን እየመራ እንደ አንድ የክልል ነጻ አውጪ ድርጅት በብሔሮች መካከል ጥርጣሬና ልዩነት እንዲሰፋ የሚያደርጉ የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካዎችንም አንግሷል። ‘እኛ እና እነሱ’ የሚል ፖለቲካን ከማካሄድ ባለፈ ‘ልዩ ኃይል’ በሚል ወታደራዊ አደረጃጀት ፈጥሮ መንግሥት መስሎ ሀገርን የማፍረስ እና የማዳከም ተግባር ውስጥ ተሳትፏል። ተቃርኖ ሁለት፦ ሰሜን እዝን ባጠቃበት ጊዜ ሕገ ወጡ ቡድን ራሱ ያደራጀውን እና ሲያሞካሸው የቆየውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 2013 ዓ.ም. በማጥቃት የተቃርኖ ጉዞውን መቀጠሉን አረጋግጧል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን እዝ የትግራይ ሕዝብ ጋሻና መከታ፣ የችግር ጊዜ ደራሽ እና ከሻዕቢያ ተከላካይ ሆኖ ላቡንና ደሙን ገብሯል። ሕገ ወጡ ቡድን የሀገር ሉዓላዊነትና የሕገ-መንግሥት ጠባቂ ነኝ ሲል ቆይቶ፣ ለ20 ዓመታት በትግራይ ሕዝብ ደህንነት ጥበቃ ላይ የነበረውን እና የትግራይ ተወላጆችንም በሠራዊቱ ውስጥ ያቀፈውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት አጥቅቷል። ሴረኛው እና በተቃርኖ የተሞላው ቡድን የማይመርዝና የማይለውጠው መሆኑን ያረጋገጠበትን ድርጊት ፈጽሞ የሀገር ጋሻና መከታን አዋርዷል። ይህ ድርጊት በኢትዮጵያ ዘመናዊ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እጅግ አሳፋሪ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል። የተቃርኖው ውጤት ግን መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ባልተጠበቀ ሁኔታ አንድ ላይ አስተሳሰረ፤ ለሉዓላዊነትና ለግዛት አንድነት የአባቶቹን ታሪክ እንዲደግም ዕድል ፈጠረ። ተቃርኖ ሦስት፦ የሰላም ውል እና የውስጥ ክፍፍል ሕገ ወጡ ቡድን የሥልጣን ጥመኝነቱን ለማርካት ስፍር ቁጥር የሌላቸው የትግራይ ክልል ተስፋ የሆኑ ወጣቶችን በጦርነት ከማገደ በኋላ የሰላም ስምምነት ተፈረመ። በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ጦርነቱን ለማስቆም የተደረገ ወሳኝ እርምጃ ነበረ። ነገር ግን ከስምምነቱ በኋላ አሁንም ከስህተቱ የማይማረው ይህ ቡድን የተቃርኖ ጉዞውን መቀጠሉን ያረጋገጠበት ጥፋት ፈጸመ። ሕገ ወጡ ቡድን ስምምነቱን በይፋ ከተቀበለው በኋላ ስምምነቱን የሚጥሱ ድርጊቶችን መፈጸም ቀጠለ። መሣሪያ ለማስረከብ ተስማምቶ በስምምነቱ መሠረት መሄድ አቃተው፣ እንቅፋት ፈጠረ። በትጥቅ ውስጥ የቆዩ ወጣቶች ወደ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመለሱ ማድረግ ነበረበት፣ አላደረገም። ይልቅስ ለሌላ ጥፋት ውስጥ ለውስጥ መዘጋጀቱን ተያያዘው። ጊዜያዊ አስተዳደር ለመመስረት ተስማምቶ ወደ ተግባር ከተገባ በኋላ የጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮችን አልቀበልም በማለት ሕገ ወጥነቱን ቀጥሎ ለትግራይ ሕዝብ ሰላም እና እፎይታ የሰጠውን የሰላም ስምምነት አፈረሰ። ከጦርነቱ ማብቃት በኋላ ትኩረት መደረግ የነበረበት የወደሙ አካባቢዎችን መገንባት፣ የተፈናቀሉትን መመለስ እና ሰብዓዊ እርዳታ ማፋጠን ላይ መሆን ሲገባው፣ ሕገ ወጡ ቡድን ወደ ውጭ ይፋ በወጣ የሥልጣን ሽኩቻና የእርስ በእርስ ውንጀላ ውስጥ መዘፈቁ ለሕዝቡ ያለው ግድየለሽነት ማሳያ ሆኖ ተወሰደ። ለጥፋት ተልዕኮው ስኬት በፍጹም የዓላማም ይሁን የትግል አንድነት የለኝም ሲላቸው ከነበሩ የጥፋት ቡድኖች ጋር አበረ። ይህ ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመመሳጠር ሉዓላዊነትን ለማስደፈር እና ሀገር ለማፍረስ በሙሉ አቅሙ መንቀሳቀስ ጀመረ። ልብ ማለት የሚገባን ባህር በርን የሚያክል ጉዳይ እንደ ተራ ሸቀጥ ያየው ቡድን እንዴት ስለ ብሔራዊ ክብር እና ሉዓላዊነት ሊያስብ ይችላል? ሊሆን አይችልም። ተቃርኖ አራት፦ የሕገ ወጡ ቡድን የመጨረሻው የጥፋት ጉዞ ዓለምና የኢትዮጵያ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ሁኔታ በከፍተኛ ሁኔታ ቢቀየርም፣ ሕገ ወጡ ሕወሓት ግን አሁንም በ1960ዎቹ እና 70ዎቹ የትግል ስልት ተከተሏል። ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከሆኑት ባዕዳን ተልዕኮ ተቀብሎ ከሀገር ውስጥ ባንዳዎች ጋር አብሯል። ‘ጽምዶ’ ከተባለው የጥፋት ስብስብ ፊት አውራሪ በመሆን የለመደውን የተቃርኖ ጉዞ ለመቀጠል ተቅበዝብዟል። የወጣቱን የሥራ፣ የዲሞክራሲ፣ የኢኮኖሚና የዘመናዊነት ጥያቄ በትክክለኛ መንገድ ከመመለስ ይልቅ ወደ ሥልጣን ለመመለስ ለሚያደርገው የቀቢጸ ተስፋ ሙከራ እያደረገ ነው። ከምርጫ ቦርድ ጋር ያለው ሕጋዊ ሰውነት የማጣት አለመግባባት እና በሕጋዊ መንገድ ራሱን ለማደስ ፈቃደኛ አለመሆኑ ቡድኑን በሕግ ፊትም ሆነ በፖለቲካዊ ምህዳሩ ውስጥ ወደ መጨረሻው የመገለልና የውድቀት ምዕራፍ መርቶታል። ዛሬ ግን ትናንት አይደለም። ኢትዮጵያ ዘመኑን በዋጀ አመራር እየተመራች ትገኛለች። ዘመኑን ሙሉ የተቃርኖ ጉዞ ያደረገው ሕገ ወጡ ቡድን ወደ መጨረሻው የፖለቲካ ውድቀት እያመራ ነው። የሕገ ወጡ ቡድን የተቃርኖ ጉዞም የበቃል።
የኢትዮጵያዊያን ምክክር፤ የጋራ ነገን የሚያሻግር የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ድልድይ
Jul 22, 2026 930
በሚኪያስ ጎቡ መግቢያ፡- ሀገራት ከጦርነት በላይ የሚፈትናቸው ጠላት አለ፤ እርሱም በአንድ ሀገር ልጆች መካከል የሚፈጠረው የመተማመን መሰናክል ነው። መሣሪያ የፈጠረውን ጉዳት እንደገና መገንባት ይቻላል። የተሰበረ ልብና የጠፋ መተማመን ግን በጉልበት አይመለስም። ለዚህም ነው ብዙ ሀገራት ከግጭት በኋላ ወደ ምክክር የሚመለሱት። ብሔራዊ ምክክር የአንድ መንግሥት ፕሮጀክት ወይም የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአንድ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፈው የሰላም ውርስ ነው። የሚጋጩ ሃሳቦች በጠመንጃ ሳይሆን በቃል ሲገናኙ፣ የተለያዩ ትርክቶች በመደማመጥ ሲቀራረቡ፣ ልዩነቶችም የጥላቻ ምንጭ ሳይሆኑ የመግባባት መነሻ ሲሆኑ ነው እውነተኛ ሀገራዊ ምክክር የሚፈጸመው። የዓለም ተሞክሮ እንደሚያሳየው ብሔራዊ ምክክር አንድ ዓይነት ቀመር የለውም። እያንዳንዱ ሀገር በታሪኩ፣ በባህሉ፣ በፖለቲካዊ እውነታውና በማኅበራዊ መዋቅሩ መሰረት የራሱን መንገድ ይመርጣል። ነገር ግን የሁሉም ግብ አንድ ነው፤ ግጭትን በመግባባት፣ ጥላቻን በመተማመን፣ ፍርሃትን በተስፋ መተካት። በአውሮፓ ከኮሙኒዝም ውድቀት በኋላ፣ በአፍሪካ ከአምባገነናዊ አስተዳደሮች ሽግግር ወቅት፣ በደቡብ አሜሪካ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሂደቶችና በዓረቡ ዓለም ከፖለቲካ አብዮቶች በኋላ የተካሄዱ ምክክሮች አንድ ትልቅ ትምህርት ይሰጣሉ። ምክክር ሲታመን ሀገር ያድናል፤ ለፖለቲካ ጥቅም ሲውል ግን ቀውስን ያባብሳል። ይህ የኢትዮጵያም ትልቁ ፈተና ነው። ሀገራዊ ምክክር የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት ነው። የምንናገረው ቃል፣ የምንጽፈው ሐሳብ፣ የምናዳምጠው አቋምና የምንቀበለው ልዩነት የነገዋን ኢትዮጵያ ይቀርጻሉ። ምክክር የሚጀምረው በአዳራሽ ሳይሆን በሰዎች ልብ ውስጥ ነው፤ የሚሳካውም ከመናገር በላይ በመደማመጥ ሲቻል ነው። ስለዚህ የዛሬው ጥያቄ "ምክክር ይካሄድ ወይ?" የሚል አይደለም። "ምክክሩን ለሀገር የሚበጅ፣ ለትውልድ የሚተርፍ፣ ለታሪክ የሚያስከብር እንዴት እናድርገው?" የሚለው ነው። መልሱም በአካታችነት፣ በእውነት፣ በመከባበርና በሀገርን ከግል ጥቅም በላይ በማስቀደም ውስጥ ይገኛል። ምክክር፤ የሀገር መድኃኒት ወይስ የትውልድ ፈተና? ምክክር ለምን ያስፈልጋል?፡- ማንኛውም ሀገር የሚያድገው በሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ግንባታ ብቻ አይደለም። በሕዝቦቿ መካከል በሚኖረው መተማመን ጭምር እንጂ። መንገድ፣ ድልድይና ፋብሪካ መገንባት ይቻላል፤ ነገር ግን የተሰበረ ማኅበራዊ ትስስር ካልተጠገነ የልማቱ መሠረት ይናወጣል። ስለዚህ ብሔራዊ ምክክር የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን የሀገር የወደፊት ዕጣ ፋንታ የሚወሰንበት የጋራ አስተሳሰብ ሂደት ነው። የምክክሩ ዋና ዓላማ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር አይደለም። ይልቁንም ሁሉም ወገኖች የራሳቸውን እውነት እየገለጹ፣ የሌላውንም እውነት በማዳመጥ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ሂደት ነው። እውነተኛ የምክክር ድል የሚለካውም የማን ሃሳብ አሸነፈ ሳይሆን ለሀገር ምን ያህል ሰላምና መተማመን ፈጠረ በሚለው ነው። የዓለም ተሞክሮ የሚያስተምረን፡- የታሪክ ገጾች እንደሚያሳዩት ሀገራት የብሔራዊ ምክክርን መንገድ የመረጡት ሌሎች አማራጮች ሲያቅቷቸው ነው። አንዳንዶቹ የረዥም ጊዜ የፖለቲካ ቀውስ ነበራቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በሥልጣን ሽኩቻ ተከፋፍለው ሲራኮቶ የሰነባበቱ ናቸው። ነገር ግን የተሳካላቸው ሀገራት አንድ የጋራ መርህ ነበራቸው፤ የሀገርን ጥቅም ከፓርቲ፣ ከቡድንና ከግል ጥቅም በላይ አስቀድመዋል። ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ወደ ዴሞክራሲ የተሸጋገረችው በበቀል ሳይሆን በሰለጠነ ምክክር ነው። ፖላንድና ሀንጋሪ የፖለቲካ ሽግግራቸውን በየጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር አሳልፈዋል። ላይቤሪያና ሊባኖስ የጦርነት ቁስላቸውን ለማዳን የመደማመጥን መንገድ መርጠዋል። በተቃራኒው ግን ምክክርን ለፖለቲካ ሕጋዊነት ማግኛ፣ ለሥልጣን ማራዘሚያ ወይም ለውጭ ጫና ማስታገሻ ብቻ ያደረጉ ሀገራት የበለጠ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። ይህም አንድ ግልጽ ትምህርት ይሰጠናል፤ የምክክር ስኬት የሚወሰነው በመድረኩ ሳይሆን በተመካካሪዎች ቅንነት መሆኑን ያስረዳናል። ምክክር የሚጠይቀው ከባድ ኃላፊነት፡- ሀገራዊ ምክክር የኮሚሽን ወይም የመንግሥት ሥራ ብቻ አይደለም። የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነትን የሚጠይቅ የጋራ ነገ አሻጋሪ ድልድይና የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ነው። ፖለቲከኛው የሀገርን ጥቅም ማስቀደም፣ የሚዲያው እውነትን በሚዛናዊነት ማቅረብ፣ የሲቪክ ማኅበራት የተገለሉ ድምፆችን ማሰማት፣ የኃይማኖት ተቋማት ይቅርታና መቻቻልን ማስፋፋት፣ ወጣቱ ከጥላቻ ይልቅ ውይይትን መምረጥና ምሁራን በማስረጃ የተደገፈ ሃሳብ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ማንም ወገን የራሱን አቋም ብቻ ለማስገደድ ከሞከረ፣ ምክክሩ ወደ ክርክር ይቀየራል። ሁሉም ለመረዳት እንጂ ለማሸነፍ ካልመጡ ደግሞ የምክክሩ መንፈስ ይጠፋል። የሀገራዊ ምክክር ትልቁ ድል የሌላውን አቋም መለወጥ ሳይሆን፣ የሌላውን ህመም መረዳት ነው። ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር፤ ልዩነታቸው ምንድን ነው?፡- ብዙ ጊዜ ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር የሚሉት ቃላት በአንድ ትርጉም ይጠቀሳሉ። ነገር ግን በፖለቲካዊና በማኅበራዊ ሂደቶች እያንዳንዳቸው የተለየ ዓላማና ባህሪ አላቸው። ይህንን ልዩነት አለማወቅ ሀገራዊ ምክክርን ከመጀመሪያው ሊያዛባው ይችላል። ውይይት የሐሳብ ልውውጥ ነው። ሰዎች ስለ አንድ ጉዳይ አመለካከታቸውን ይገልጻሉ፣ ይደማመጣሉ። ሁልጊዜ ውሳኔ ላይ ላይደርስ ይችላል። ክርክር የሚያተኩረው የማን ሃሳብ ትክክል እንደሆነ ላይ ነው። የራስን አቋም በማስረጃ ለማስረዳት ይደረጋል፤ አንድ አሸናፊና አንድ ተሸናፊ ሊኖር ይችላል። ድርድር ደግሞ የጥቅም ግጭትን በመካከለኛ መፍትሔ ለመፍታት የሚደረግ ሂደት ነው። እያንዳንዱ ወገን ከአቋሙ በመቀነስ የጋራ መፍትሔ ለማግኘት ይሞክራል። ሀገራዊ ምክክር ግን ከእነዚህ ሁሉ የላቀ ሂደት ነው። ዓላማው ማንንም ማሸነፍ ወይም ማስሸነፍ ሳይሆን የሀገር የወደፊት አቅጣጫ ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። በምክክር ውስጥ የሚሸነፍ ሰው የለም፤ የሚያሸንፈው ሀገር ነው። የኢትዮጵያ ልዩ እውነታ፡- ኢትዮጵያ ሦስት ሺህ ዘመናትን የተሻገረ በሕብር ያሸበረቀ ታሪክ፣ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና ኃይማኖት ያላት ሀገር ናት። ይህ በሕብር ያሸበረቀ ልዩነት የኢትዮጵያ ጥንካሬ መሆን ሲገባው በተለያዩ ወቅቶች የፖለቲካ አለመግባባቶችና የታሪክ ትርክቶች የመከፋፈል መሣሪያ ሆነው ቆይተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ፈተናም ይህ ነው። ሁሉም የራሳቸውን ታሪክ ይዘው ወደ ጠረጴዛው ይመጣሉ፤ ነገር ግን ከጠረጴዛው የሚወጡት አንድ የጋራ የወደፊት ርዕይ ይዘው መሆን አለባቸው። ይህ ቀላል አይደለም። ስለዚህ ምክክሩ ከቃላት በላይ በተግባር የሚገለጥ ቅንነትን ይፈልጋል። የዋናው ምክክር ጉባኤ የህዝብ ወኪል ተመካካሪዎችም ሀገርን የማስቀደም ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ስኬታማ ምክክር የሚመሰረትባቸው አምስት ምሰሶዎች፡- ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን ቢያንስ አምስት መሠረታዊ ምሰሶዎች ሊኖሩት ይገባል። እነሱም መተማመን፣ አካታችነት፣ እውነት፣ ፍትሕና የጋራ ርዕይ ናቸው። ከሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበራሰብ የሕዝብ ወኪል 4 ሺ ተመካካሪ ኢትዮጵያዊያንም በሀገር ግንባታ ጉዳይ፣ የመንግስት አደረጃጃትና ስርአት ጉዳይ፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬድዋ ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና የመልካም አስተዳዳር ጉዳዮች፣ የሰላም ግንባታ ጉዳዮች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽ ማዕከል እየመከሩ ይገኛል። ሀገራዊ ምክክር ያለፈውን ለመቁጠር ሳይሆን፣ የወደፊቱን ለመገንባት የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው። የኢትዮጵያ መንገድም የልዩነት ግድግዳን የሚያፈርስ የትውልድ አደራና የብሔራዊ መግባባት ማሰሪያ ጥበብና ትልም ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፤ የተገኙ ዕድሎች፣ ዋና ፈተናዎች እና የወደፊት አቅጣጫ በታሪክ ጉዞዋ ውስጥ ኢትዮጵያ ብዙ የፈተና ዘመናትን አልፋለች። አንዳንዶቹ ፈተናዎች ከውጭ ጥቃት የመጡ ቢሆኑም፣ አብዛኞቹ ግን ከውስጣዊ አለመግባባቶች፣ ከተለያዩ የታሪክ ትርክቶች፣ ከፖለቲካ ፉክክርና ከመተማመን እጥረት የተፈጠሩ ናቸው። ስለዚህ የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት የዛሬን ችግር ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፣ የትውልድ ዕዳን ለማቃለል የተጀመረ ታሪካዊ ሂደት ነው። ይህ ሂደት ቀላል አይደለም። በርካታ ዓመታት የተከማቹ ቅሬታዎች፣ የተለያዩ እውነታዎች፣ የተቃራኒ ትርክቶችና የተለያዩ የፖለቲካ ፍላጎቶች በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መገናኘታቸው በራሱ ትልቅ ፈተና ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ ትልቁ ፈተና ልዩነትን ወደ መግባባት መቀየር ነው። ዕድሎች፤ ሊጠቀሙባቸው የሚገቡ ወሳኝ መስኮቶች፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ የምታነሳበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። የታሪክ አተረጓጎም፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የሥልጣን ክፍፍል፣ የሀብት አጠቃቀም፣ የፍትሕ ጉዳዮችና የአብሮነት ዕሴቶች በጦርነት ሳይሆን በሐሳብ የሚፈቱበት ዕድል ይፈጥራል። ከዚህም በላይ ምክክሩ የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር የሚያስችል ዕድል ነው። ለብዙ ዓመታት "አሸናፊና ተሸናፊ" በሚለው አስተሳሰብ የተመራውን ፖለቲካ ወደ "አብሮ ማሸነፍ" የሚሸጋግር ከሆነ እውነትም የኢትጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ ጠንካራ መሠረት ያገኛል። በሂደቱ ፊት የሚቆሙ ፈተናዎች፡- ማንኛውም ሀገራዊ ምክክር ከፍተኛ ተስፋ እንደሚፈጥር ሁሉ ከባድ ፈተናዎችንም ይዞ ይመጣል። የመጀመሪያው ፈተና የመተማመን እጥረት ነው። ለብዙ ዓመታት የተገነባ ጥርጣሬ በጥቂት ወራት አይጠፋም። ስለዚህ የምክክሩ ተዓማኒነት በእያንዳንዱ እርምጃ ሊገነባ ይገባል። ሁለተኛው ፈተና የተለያዩ የታሪክ ትርክቶች ናቸው። አንድ ክስተት በአንዱ ወገን የድል ታሪክ ሲሆን፣ በሌላው ወገን የመከራ ታሪክ ሊሆን ይችላል። ይህን ልዩነት በክብር መቀበል እንጂ መግፋት አይቻልም። በሌላ መልኩም የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ ስርጭት ነው። በዲጂታል ዘመን አንድ ያልተረጋገጠ መረጃ በጥቂት ደቂቃዎች ሺዎችን ሊደርስ ይችላል። ስለዚህ የሚዲያ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሚወስዱት ኃላፊነት ከመቼውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። የምሁራንና የመገናኛ ብዙኅን ሚና፡- በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ምሁራን ስሜትን ሳይሆን ማስረጃን ማቅረብ አለባቸው። የማኅበረሰብ ችግሮችን በሳይንሳዊ ጥናት መተንተን፣ ከሌሎች ሀገራት ልምድ መማርና አማራጭ መፍትሔዎችን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። መገናኛ ብዙኅንም በዚህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው። መገናኛ ብዙኅን ወሬን ከማባዛት ይልቅ እውነትን ማጣራት፣ ልዩነትን ከማባባስ ይልቅ መግባባትን ማጎልበት፣ ስሜትን ከማቀጣጠል ይልቅ እውነታን ማቅረብ አለበት። ምክክሩን የሚያጠናክር የመገናኛ አውታር ታሪክ ይሠራል፤ የሚያደናቅፍ ደግሞ በታሪክ ይጠየቃል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ቀን የሚጠናቀቅ ክስተት አይደለም። ምክክር በትውልድ የሚገነባ የፖለቲካ ባህል ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራውን ሊጨርስ ይችላል፤ ነገር ግን የመደማመጥ ባህል በሕዝብ ውስጥ ካልሰረጸ የምክክሩ እውነተኛ ዓላማ አይሳካም። የዛሬ ውሳኔ፤ የነገ ኢትዮጵያ፡- አንዳንድ የታሪክ ወቅቶች በየቀኑ አይመጡም። አንዳንድ ውሳኔዎችም የአንድ መንግሥት ዘመንን ብቻ ሳይሆን የትውልዶችን ዕጣ ፈንታ ይወስናሉ። ሀገራዊ ምክክር የእነዚህ ታሪካዊ ውሳኔዎች አንዱ ነው። ዛሬ በምንመርጠው የምክክር ባህል፣ በምንገነባው መተማመንና በምናሳየው የፖለቲካ ብስለት ላይ የነገዋን የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ተምሳሌት ኢትዮጵያ ያንፃል። ምክክር ሁሉንም ችግር በአንድ ጊዜ የሚፈታ አስማታዊ መፍትሔ አይደለም። ነገር ግን ጦርነትን ከውይይት፣ ጥላቻን ከመቻቻል፣ መከፋፈልን ከመተባበር የሚተካ ብልህ መንገድ ነው። የሚያደርገውም ልዩነቶችን ማጥፋት ሳይሆን ልዩነቶችን በአንድ ሀገር ጣሪያ ስር እንዴት እንደሚኖሩ የጋራ ሕግና ሥርዓት መፍጠር ነው። በእርግጥ ኢትዮጵያ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፋለች። የፖለቲካ አለመተማመን፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የፀጥታ ችግሮች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎችና የማኅበራዊ ስብራቶች በቀላሉ የሚያልፉ አይደሉም። ይሁን እንጂ እነዚህን ችግሮች በጥይት ከመፍታት ይልቅ በምክክር ለመፍታት መሞከር በራሱ የታሪክ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ ግን የአንድ ተቋም ብቻ አይደለም። የመንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኅን ተቋማት፣ የምሁራን፣ የወጣቶች፣ የሴቶችና የእያንዳንዱ ዜጋ የጋራ ኃላፊነት ነው። የሀገር ዕጣ ፋንታ ለአንድ ቡድን ብቻ የሚተው አይደለም፤ በጋራ የሚገነባ እንጂ። ከምክክር ወደ ባህል፡- ምክክሩ ተጠናቀቀ ማለት የሀገሪቱ ችግሮች ተፈቱ ማለት አይደለም። እውነተኛው ስኬት የሚለካው የመደማመጥ ባህል በማኅበረሰቡ ውስጥ ሲሰርጽ ነው። በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመገናኛ ብዙኅን፣ በፖለቲካ ተቋማትና በየቤቱ የመነጋገር ባህል ካልጠነከረ፣ ምክክሩ የሰነድ ውጤት ብቻ ሆኖ ይቀራል። የእውነተኛ ዴሞክራሲ መሠረት ተመሳሳይ አስተሳሰብ መኖር አይደለም፤ የተለያዩ አስተሳሰቦችን በሰላም የመቀበል ባህል መኖር ነው። ልዩነት የችግር ምንጭ ሳይሆን የጥንካሬ ምንጭ ሲሆን ነው አንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም የምታገኘው። የማጠቃለያ፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚያስፈልገው ብልህ አመራር ብቻ አይደለም፤ ታጋሽ ዜጎችንም ይፈልጋል። ሀገር የምትገነባው በግንብ ሳይሆን በመተማመን ነው። ሰላም የሚጸናውም በፍርሃት ሳይሆን በፍትሕ ነው። ዛሬ የምንመርጠው የምክክር መንገድ ነገ ለልጆቻችን የምንተወው ታሪክ ይሆናል። ስለዚህ በኢትዮጵያን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተደራጅተው የሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የዛሬ አጀንዳ ብቻ አይደሉም፤ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚቀርጽ የትውልድ አደራ እንጂ። የዋናው ምክክር ጉባኤ ተመካካሪ የሕዝብ ወኪሎችም ከግልና ቡድን ፍላጎት ይልቅ የቀጣዩን ትውልድና ሀገርን ማስቀደም ይጠበቅባቸውል። ምክክር የቃላት ልውውጥ ብቻ አይደለም፤ የተሰበረ መተማመንን የሚጠግን፣ የተከፋፈለ ማኅበረሰብን የሚያቀራርብ፣ የትውልድ ታሪክን በአዲስ ተስፋ የሚጽፍ ሀገራዊ ጥበብ ነው። የምንወስነው ዛሬ የምንወርሰውን ነገ ይበይናል። ምክክር የሀገር መድኅን ነው፤ ኢትዮጵያም እየመከረች ነው።      
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 1033
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 11453
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 21346
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14373
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20125
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 103585
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 78563
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57167
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 54741
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 39251
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 39006
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 38488
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 37213
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 103585
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 78563
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57167
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 54741
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 990
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።
ዓይነ ስውሩ የቧንቧ ሰራተኛ 
Jul 31, 2026 1174
ዋግ ኽምራ፤ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ) ፦"ዓይኖቼ ማየት ባይችሉም እጆቼ ተዓምር ይሰራሉ'' -ዓይነ ስውሩ የቧንቧ ሰራተኛ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ መለስ ጌታነህ የ62 ዓመት የእድሜ ባለጸጋ አዛውንት ናቸው፤ ከጊዜ በኋላ በመጣ ችግር የሁለት ዓይኖቻቸውን ብርሃን ያጡ ቢሆንም በአካባቢው ስመ ጥር የቧንቧ ሠራተኛ ናቸው። ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ ገና በወጣትነት ዕድሜያቸው የቧንቧ ሥራ ሙያን ቀስመው፣ በዋግ ኽምራ በሚገኙ ወረዳዎች በመንቀሳቀስ ለንጹሕ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት አሻራቸውን እያሳረፉ ያሉ ትጉህ ባለሙያ ናቸው። ቆላ በመውረድ፣ ደጋ በመውጣት፣ ተራራና ሸንተረሩን ሳይበግራቸው የውሃ መስመር በመዘርጋት ህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ እንዲደርሰው እያደረጉ ያሉ አዛውንት ናቸው። ለዚህም በተደጋጋሚ የምስጋና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በ1991 ዓ.ም የተፈራ ኃይሉ መታሰቢያ ጠቅላላ ሆስፒታል ሥራ ሲጀምር እሳቸው በቧንቧ ባለሙያነት በቋሚነት በመቀጠር፣ የውሃ መስመር በመዘርጋትና በመጠገን የሕክምና ክፍሎች ያልተቋረጠ ውሃ እንዲያገኙ ማድረግ ችለዋል። ይሁን እንጂ ከዕለታት በአንድ ቀን ሥራቸውን እያከናወኑ ባሉበት ወቅት ባላወቁት ምክንያት የሁለት ዓይኖቻቸውን ብርሃን ያጡበት አጋጣሚ በመከሰቱ ከቤት ለመዋል መገደዳቸውን ያወሳሉ። እንደ አቶ መለስ ገለጻ፡ “ዓይኔ ማየት ባለመቻሉ ራሴን ችዬ መንቀሳቀስ፣ እንደልቤ ሜትር ዘርግቼ ለክቼ መቁረጥና ገደል ላይ ተንጠልጥዬ የቧንቧ መስመር መዘርጋት አልችልም የሚል የተሸናፊነት ስሜት አድሮብኝ ተስፋ ቆርጬ ተቀምጬ ነበር” ይላሉ። በዚህ ወቅት ትጋታቸውንና ብርታታቸውን የሚያውቁ የሆስፒታሉ ዳይሬክተር የነበሩት ዶክተር ዓለማየሁ ትኩ፣ ወደ ሆስፒታሉ በመውሰድና በመምከር ሥራቸውን እንዲቀጥሉ እንዳገዟቸው አውስተዋል። ቀስ በቀስም አቶ መለስ ሜትር በመዘርጋትና መጋዝ በመጨበጥ ልኬታን አስተካክለው፣ መገጣጠሚያ ቦታዎችን በዳበሳ ለይተው የቧንቧ ሙያ ሥራቸውን እንደገና “ሀ” ብለው ማስቀጠላቸውን አመልክተዋል። ምንም እንኳን ከወረዳ ወረዳ ተንቀሳቅሶ መሥራት ባይችሉም፣ በግለሰብ ቤቶችና ድርጅቶች እየተንቀሳቀሱ የቧንቧ ጥገና ሥራቸውን በብቃት እያከናወኑ ያሉ ብቁ ባለሙያ ሆነው ቀጥለዋል። በሆስፒታሉም ከአገልግሎት ውጭ የነበሩ የውሃ መስመሮችን በመለየትና በአግባቡ በመጠገን፣ ለሐኪሞችና ለሕመምተኞች ወጥ የሆነ የንጹሕ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ “አንቱ” የተባሉ ባለሙያ ሆነዋል። አቶ መለስ በቧንቧ ሥራ ሳይገደቡ፣ በራዲዮ በሚቀርቡ የቴክኖሎጂ ፕሮግራሞች ባገኙት እውቀት ከአገልግሎት ውጭ የነበረውን የሆስፒታሉን የላውንድሪ (ልብስ ማጠቢያ) ማሽን በዳበሳ ጠግነው ወደ አገልግሎት በመመለስ ሆስፒታሉን ከወጪ ታድገዋል። “ብርሃን ከዓይን ብቻ ሳይሆን ከልብና ከመዳፋችንም ይገኛል” የሚሉት አቶ መለስ፣ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ምጣዶችን በመጠገንና ሌሎችንም የቴክኒክ ሥራዎች በመሥራት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን የሚያስተዳድሩ ጠንካራ የዕድሜ ባለፀጋ ናቸው። "የዓይን ብርሃኔን አጣሁ ብዬ አንድም ቀን አስቤ አላውቅም” የሚሉት አቶ መለስ፣ አሁን ላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ጣራ ላይ በመውጣት ጭምር ቧንቧ ጠግነው የሚወርዱ ባለሙያ ሆነዋል። “እኔ ሥራ ሳልሠራ ስውል ያመኛል” የሚሉት አቶ መለስ፣ ወጣቱ ሥራን ሳይንቅ ከሰራ ከትንሽ ነገር ተነስቶ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም ትልቅ ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚችል ምክራቸውን ለግሰዋል። ስለ ጉዳዩ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተፈራ ኃይሉ ጠቅላላ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምሩ ቢምረው እንዳሉት፡ ጋሽ መለስ የዓይን ብርሃናቸውን ቢያጡም በሙያቸው የትጋትና የ“ይቻላል” ተምሳሌት የሆኑ አዛውንት ናቸው። አዛውንቱ በሙያቸው የሆስፒታሉ የውሃ አቅርቦት እንዳይቋረጥ በማድረግ ለሕክምና ሥራ መቀላጠፍ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸው ለሌሎች ባለሙያዎች በታታሪነት፣ በሥራ ፍቅር እና በጥንካሬ አርዓያ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም