ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በደሴ ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የስራ መስኮች ላይ የተሰማሩ ሴቶች ውጤታማ መሆን ችለዋል
Oct 21, 2025 10
ደሴ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፡ - በደሴ ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የስራ መስኮች የተሰማሩ ሴቶች ውጤታማ መሆናቸውን ተናገሩ። የክልሉ፣ የዞንና የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴት አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በደሴ ከተማ በልማት ሕብረት በተደራጁ ሴቶች የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የሴቶቹ የስራ ዘርፎች የባልትና ውጤቶችና የሌማት ትሩፋት መርሃ ገብርን ጨምሮ ሌሎችም ይገኙበታል። በሴቶች የልማት ሕብረት ሶስት ሆነው በመደራጀት በባልትና ስራ ላይ ከተሰማሩት መካከል ወይዘሮ ዘሪቱ ጌታቸው፤ የተለያዩ የባልትና ውጤቶችን በማዘጋጀት ለገበያ በማቅረብ ትርፋማ መሆናቸውንና ለ30 ሴቶችም የሥራ እድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግረዋል። ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ አሊማ አስፋው የከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸላቸው መሬት የተለያዩ አትክልቶችን በማልማት ከቤት ፍጆታ አልፈው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። በወተት ላም እርባታ ላይ የተሰማሩት ወይዘሮ ወርቄ ከልካይም፤ በቀን ከ400 ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። በጥቂት ላሞች የጀመሩት ስራ አሁን ላይ ቁጥራቸው ጨምሮ 43 መድረሱን ጠቅሰው ፤ ስራውን አጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ምሳዬ ከድር፤ በሴቶች ልማት ሕብረት ከ71 ሺህ በላይ ሴቶች ተደራጅተው ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸው፤ በየተሰማሩባቸው ዘርፎችም ውጤታማ ሆነዋል ብለዋል። የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ዝና ጌታቸው በበኩላቸው፤ ሴቶችን በማደራጀት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ ረገድ የተጀመሩ ጥረቶች ውጤት እያታየባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትም ባለፈ በፖለቲካና ማህበራዊ ዘርፎችም ጠንካራ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ይሰራል ሲሉ አረጋግጠዋል።
በክልሉ በስርዓተ ፆታ አካታችነት በማጠናከር የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ ነው
Oct 21, 2025 25
አዳማ፤ ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ የስርዓተ ፆታ አካታችነት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ገለፀ። ቢሮው በክልሉ በስርዓተ ፆታ እኩልነት አተገባበርና በታዩ ውስንነቶች ላይ ከኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርስቲና ከክልሉ የስራ ዕድል ፈጠራ ቢሮ ጋር በመተባበር ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የምክክር መድረክ በአዳማ አካሄዷል። የኦሮሚያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በክልሉ የስርዓተ ፆታ እኩልነትን ከማረጋገጥ አንጻር የሚታዩ ውስንነቶችን ለመፍታት ትኩረት ተደርጓል። በተለይ በክልሉ የመንግሥት መዋቅሮች የስርዓተ ፆታ እኩልነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም የህፃናትን መብትና ደህንነት የማስጠበቅ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በዚህም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ማነቆ የሆኑ ችግሮች እየተፈቱ መሆኑንም ተናግረዋል። ሴቶች ከኢኮኖሚ ጥገኝነት እንዲላቀቁና ራሳቸውን እንዲችሉ በግብርና፣ በአገልግሎትና በተለያዩ የስራ መስኮች ተሳትፏቸው እንዲጎለብት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በበጎ ፈቃድ አገልግሎትም ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል። የዛሬው መድረክም በክልሉ መንግሰት መዋቅር ውስጥ በስርዓተ ፆታ እኩልነትና ተግባራዊነት ላይ የተገኙ ውጤታማ ተሞክሮዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና የተለዩ ክፍተቶችን ለመሙላት በጋራ ዕቅድ የተደገፈ የተቀናጀ ርብርብ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል። በጨፌ ኦሮሚያ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ መስታወት ፈይሳ፣ የምክር ቤት አባላቱ በዕቅድና በመስክ ምልክታ የሴቶችን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንፃር አበረታች ስራዎች እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ ከዕቅድ ጀምሮ ከወረዳ እስከ ክልሉ የመንግስት መዋቅር ድረስ በየደረጃው ባለው ተቋማት የስርዓተ ፆታ እኩልነት ትግበራ ላይ ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል። ''የስርዓተ ፆታን ተግባራዊነት ከማረጋገጥ አንፃር ከተቋም ተቋም ልዩነት ቢኖርም መሻሻል አለ'' ያሉት ሰብሳቢዋ በተለይ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ከማረጋገጥና ሴቶች ወደ ውሳኔ ሰጪነት እንዲመጡ ከማድረግ አንፃር አበረታች ውጤት እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ በስራ ዕድል ፈጠራና ሴቶች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ በተቀናጀ መልኩ መሰራት እንዳለበትም አመለክተዋል። የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርስቲ ተመራማሪ አቶ ሀብታሙ ደሳለኝ በበኩላቸው የስርዓተ ፆታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ እና በዕቅድ የሚመራ ስራ ማከናወን ያስፈልጋል ብለዋል። በስርዓተ ፆታ ተግባራት ዙሪያ ያለው ግንዛቤ በሁሉም መልኩ ማደጉ፣ የሴቶች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ውሳኔ ሰጪነት ሚና እያደገ መምጣቱ አበረታች ጥረት መሆኑን አስረድተዋል። በዩኒቨርስቲው አማካኝነት በስርዓተ ፆታ እኩልነትና ተግባራዊነት ላይ አተኩሮ ጥናት መካሄዱን ገልጸው በጥናቱ መሰረትም መሻሻሎች ቢኖሩም በርካታ ስራዎች ይቀራሉ ብለዋል።
ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ከአሜሪካ የግምጃ ቤት እና ስቴት ዲፓርትመንት የስራ ሀላፊዎች ጋር የኢኮኖሚ ትብብርን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መከሩ
Oct 21, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፦ በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ ከአሜሪካ የግምጃ ቤት እና ስቴት ዲፓርትመንት የስራ ሀላፊዎች ጋር የኢኮኖሚ ትብብርን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። ውይይቱ የተካሄደው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብሰባ ጎን ለጎን ነው። በውይይቱም አቶ አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያን ወቅታዊ የልማትና ዕድገት ሁኔታ እንዲሁም የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ሂደትን የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግስት ግልጸኝነትን ለማስፈን፣ የመንግስት አስተዳደርን ለማጠናከርና የቢዝነስና ኢንቨስትመንት ምህዳሩን የበለጠ ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅሞች በሆኑ ማለትም አሜሪካ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም የምታደርገውን ድጋፍ በተለይ በባለብዙ ወገን ባንኮችና በዓለም ገንዘብ ድርጅት በኩል እንዲሁም በንግድና ኢንቨስትመንት ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተመላክቷል። የአሜሪካ የስራ ሀላፊዎች በበኩላቸው አሜሪካ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤታማነት የቴክኒክ ድጋፍን ጨምሮ በግሉ ዘርፍ በመሳተፍ እና ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር በመተባበር የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። ሁለቱ ወገኖች ቀዳሚ በሆኑና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ በሚያስችሉ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮቻቸው ላይ የሚያደርጉትን ውይይት አጠናክሮ ለማስቀጠል ተስማምተዋል።
የሕዳሴ ግድብ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁሞ መጨረስ እንደሚቻል አሳይቷል፤ የቀድሞ ትርክትን ቀይሯል
Oct 21, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ጫናዎችን ተቋቁማ መፈጸም እንደምትችል ያሳየ፤ ዓባይ ግንድ ይዞ ይዞራል የሚለውን ትርክት የቀየረ ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ኮሚቴ እና አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም የጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አማረች በካሎ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ እንድትታይ አድርጓል፡፡ ለዘመናት ሲነገር የቆየው "ዓባይ ግንድ ይዞ ይዞራል" የሚለው ትርክት በአዲስ አስተሳሰብ በመቀየር የኢትዮጵያውያንን መቻል ገልጧል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን የትኛውም ዓለም አቀፍ ጫና ሳይበግራት መፈጸም እንደምትችል ማረጋገጫ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ሀብታችንን በፍትሐዊነት በመጠቀም ለቀጣናው ልማትና ትስስር በጋራ እንድምንሰራ ዳግም ያረጋገጥንበት ፕሮጀክታችንም ነው ብለዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጆ፤ የሕዳሴ ግድብ ህዝቡን በፈቃደኝነት ማነሳሳት ትልቅ የፋይናንስ አቅም መሆኑን አረጋግጧል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመላቀቅ በራሷ የበጀት አቅም ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረግ እንድምትችል ማስተማሪያ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በውጭ ብድር ቢጀመር ኖሮ ለዘመናት እንደቆመ ይቀራል እንጂ አይጠናቀቅም ነበር ብለዋል፡፡ በግንባታ ወቅት ሲደርሱ የቆዩት ዓለም አቀፍ ጫናዎች ትልቅ ማሳያዎች ናቸው ያሉት ሰብሳቢው፤ የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ አቅሟን ያሳየችበት ለነገ ልምድ የወሰደችበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምክር ቤቱ የውሃ፣ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች እና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፈቲያ አህመድ በበኩላቸው፤ የሕዳሴ ግድብ የመላ ኢትዮጵያውያን የላብ የደምና የእንባ ጠብታ ድምር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሕዳሴ የኢትዮጵያውያን አንድነትና ትብብር ማጠናከሪያ፣ የአይበገሬነት ማሳያ እና የቁርጠኝነታቸው ማረጋገጫ ነው ብለዋል፡፡ በሁሉም የዓለም ማዕዘን ያሉ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከአርሶ አደር እስከ አርብቶ አደር፣ ከነጋዴ እስከ መንግስት ሰራተኛ ያወጡት ገንዘብ ባክኖ እንዳልቀረ ማሳያ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ከሁሉም ኢትዮጵያውያን በተዋጣ ሀብት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እንደተጠናቀቀ ሁሉ ሌሎች ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ለመጨረስ መረባረብ ይገባናል ብለዋል፡፡
በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Oct 21, 2025 60
ሆሳዕና ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ) :- በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቷ የሚስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ኮሚሽኑ ከዝግጅት ምዕራፍ በመጀመር በሁሉም አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አሁን ላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ እያካሄደ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ሂደት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ሁሉን አቀፍና አካታች የውይይት ሂደትን አጠናክሮ የቀጠለ መሆኑንም ማረጋገጥ ይቻላል። ከዚህ አንፃር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የምክክር ሂደቱ የሀገርን ችግር በባለቤትነት በመያዝ በምክክር መፍታት የምንችልበት ታሪካዊ አጋጣሚ ላይ እንገኛለን ብለዋል። የኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች በውይይት ለመፍታት በሚደረገው ታሪካዊ አጋጣሚ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ አረጋግጠዋል። በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የቁጥጥር መምሪያ ኃላፊና የሆሳዕና ደብረ መዊዕ ገዳም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቢ ትፍስኢት ቀሲስ ዳዊት አብርሃም፤ ለችግሮች ሁሉ መፍቻ መንገድ ከውይይት የበለጠ አዋጭና አትራፊ መንገድ የለም ይላሉ። በመሆኑም የሀገርን ችግሮች ተመካክሮ በመፍታት ለትውልዱ ሁሉ የተመቸችና ሰላም የሰፈነባት ሀገር ማጽናት የጋራ አደራና ሃላፊነታችን ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስትና ዜጎች ያለችግር የሚኖሩባት ሀገር ለመገንባት ያለ ልዩነት ለምክክር መሰባሰብ አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የአብሮነትንና የሰላም እሴቶችን ማጠናከር እንዲሁም ሰላምን ማስተማር የኃይማኖት አባቶች ዋነኛ ተልዕኮ መሆኑን አንስተው ለምክክሩ መሳካት የላቀ ሚናችንን ለመወጣት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የወጣቶች ተወካይ እስማኤል ሻሜቦ፤ በበኩሉ በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት እየሰራን እንገኛለን ይህንኑም አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ኮሚሽኑ የጀመራቸውን ስራዎች በማገዝ ረገድ በተለይም ቤተ እምነቶች ከፍተኛ ሃላፊነት ያለባቸው በመሆኑ በዚሁ ልክ ለማገዝ ተዘጋጅተናል ሲልም አረጋግጧል። የቡታጅራ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ላቀች ወሰኔ፤ በሀገር ጉዳይ ላይ ተቀራርበን በመወያየት ችግሮችን መፍታት ባለመቻላችን ብዙ ዋጋ ያስከፈለን በመሆኑ አሁን ላይ ሁላችንም ለምክክር ዝግጁ መሆን አለብን ብለዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ለሀገር ሰላም፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነትና ለልማት እቅዶች ስኬት በጋራ መትጋት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል። "እኛ ኢትዮጵያውያን በአብሮነት በመጓዝ ወደ ተሻለ ምዕራፍ እንድንደርስ የውስጥ ችግሮቻችንን በመነጋገርና በመወያየት የመፍታት ባህላችንን ማዳበር አለብን" ያሉት የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ምህረት ተስፋዬ ናቸው፡፡ የጠመንጃ ትግል ኪሳራ እንጂ ትርፍ የሌለው በመሆኑ የሰላምን አማራጭ ብቻ በመከተል በምክክር ለችግሮች መፍትሄ ይዘን መቅረብ ይጠበቅብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን "የሴቶች፣ የወጣቶችና የአካል ጉዳተኞች ሚናና አስተዋጽኦ ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር " በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ክልሎች የውይይት መድረኮች በመካሄድ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
ፖለቲካ
በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Oct 21, 2025 60
ሆሳዕና ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ) :- በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቷ የሚስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ኮሚሽኑ ከዝግጅት ምዕራፍ በመጀመር በሁሉም አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አሁን ላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ እያካሄደ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ሂደት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ሁሉን አቀፍና አካታች የውይይት ሂደትን አጠናክሮ የቀጠለ መሆኑንም ማረጋገጥ ይቻላል። ከዚህ አንፃር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የምክክር ሂደቱ የሀገርን ችግር በባለቤትነት በመያዝ በምክክር መፍታት የምንችልበት ታሪካዊ አጋጣሚ ላይ እንገኛለን ብለዋል። የኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች በውይይት ለመፍታት በሚደረገው ታሪካዊ አጋጣሚ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ አረጋግጠዋል። በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የቁጥጥር መምሪያ ኃላፊና የሆሳዕና ደብረ መዊዕ ገዳም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቢ ትፍስኢት ቀሲስ ዳዊት አብርሃም፤ ለችግሮች ሁሉ መፍቻ መንገድ ከውይይት የበለጠ አዋጭና አትራፊ መንገድ የለም ይላሉ። በመሆኑም የሀገርን ችግሮች ተመካክሮ በመፍታት ለትውልዱ ሁሉ የተመቸችና ሰላም የሰፈነባት ሀገር ማጽናት የጋራ አደራና ሃላፊነታችን ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስትና ዜጎች ያለችግር የሚኖሩባት ሀገር ለመገንባት ያለ ልዩነት ለምክክር መሰባሰብ አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የአብሮነትንና የሰላም እሴቶችን ማጠናከር እንዲሁም ሰላምን ማስተማር የኃይማኖት አባቶች ዋነኛ ተልዕኮ መሆኑን አንስተው ለምክክሩ መሳካት የላቀ ሚናችንን ለመወጣት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የወጣቶች ተወካይ እስማኤል ሻሜቦ፤ በበኩሉ በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት እየሰራን እንገኛለን ይህንኑም አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ኮሚሽኑ የጀመራቸውን ስራዎች በማገዝ ረገድ በተለይም ቤተ እምነቶች ከፍተኛ ሃላፊነት ያለባቸው በመሆኑ በዚሁ ልክ ለማገዝ ተዘጋጅተናል ሲልም አረጋግጧል። የቡታጅራ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ላቀች ወሰኔ፤ በሀገር ጉዳይ ላይ ተቀራርበን በመወያየት ችግሮችን መፍታት ባለመቻላችን ብዙ ዋጋ ያስከፈለን በመሆኑ አሁን ላይ ሁላችንም ለምክክር ዝግጁ መሆን አለብን ብለዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ለሀገር ሰላም፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነትና ለልማት እቅዶች ስኬት በጋራ መትጋት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል። "እኛ ኢትዮጵያውያን በአብሮነት በመጓዝ ወደ ተሻለ ምዕራፍ እንድንደርስ የውስጥ ችግሮቻችንን በመነጋገርና በመወያየት የመፍታት ባህላችንን ማዳበር አለብን" ያሉት የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ምህረት ተስፋዬ ናቸው፡፡ የጠመንጃ ትግል ኪሳራ እንጂ ትርፍ የሌለው በመሆኑ የሰላምን አማራጭ ብቻ በመከተል በምክክር ለችግሮች መፍትሄ ይዘን መቅረብ ይጠበቅብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን "የሴቶች፣ የወጣቶችና የአካል ጉዳተኞች ሚናና አስተዋጽኦ ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር " በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ክልሎች የውይይት መድረኮች በመካሄድ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት በሁሉም መስኮች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ ናቸው
Oct 21, 2025 128
ጎንደር ፤ ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ)፡ በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት በሁሉም መስኮች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ መሆናቸውን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የጎንደር ከተማ አስተዳደር የበጀት ዓመቱ ሶሰት ወራት የፓርቲ እና የመንግሥት የስራ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ እና የአማራ ክልል የከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)፤ በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት በሁሉም መስኮች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከዚህ አንፃር በጎንደር ከተማ የተከናወኑ የመሰረተ ልማትና የፕሮጀክቶች ግንባታዎች ጥሩ አፈፃፀም የታየባቸው መሆኑን አንስተው የመንግሥት ተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ ምቹ እና የተቀላጠፈ በማድረግ የህዝብን እንግልት ለማስቀረት የተከናወኑ ተግባራትም የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በጎንደር ከተማም እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ፈጠራን፣ የፍጥነትን፣ ጥራትና አዲስ የስራ ባህል ለውጥን በማምጣት አበረታች ውጤት የታየባቸው መሆናቸውን ገልጸዋል። በኮሪደር ልማት፣ በቅርስ ጥገናና እድሳት፣ በስራ እድል ፈጠራና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የተመዘገቡት ውጤቶች ሰላምን በጋራ በማረጋገጥ የመጣ ውጤት መሆኑን አስረድተዋል። እንደ አጠቃላይ የክልሉ መንግስት የቀጣይ 25 ዓመት አሻጋሪ የልማት እቅድ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀቱንም ዶክተር አሕመዲን ጠቁመዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው፤ በከተማ አስተዳደሩ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ሰላምን በማስጠበቅ የተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች በውጤት የተለኩና የህዝቡንም እርካታ በተጨባጭ ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። የዛሬ መድረክም የተሳኩ እቅዶችን የምናጠናክርበት፣ ደካማ አፈጻጸሞችን የምናርምበትና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ መግባባት በመፍጠር የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የምንተጋበት ነው ሲሉ ገልጸዋል። በመድረኩ የክልሉና በየደረጃው የሚገኙ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በባሕርዳር ከተማ ከሕብረተሰቡ ጋር የተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን አስችሏል
Oct 21, 2025 99
ባሕርዳር፤ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ) ፡-በባሕርዳር ሕብረተሰቡን በማስተባበር የተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር በከተማዋ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ማስቻሉን የከተማው አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ። በአማራ ክልል በየደረጃው ሲካሄዱ በቆዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሕብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ሰላምን ለማጽናት ያለውን የፀና አቋም በተግባር እያሳየ ነው። ይህንን በቁርጠኝነት በተግባር እያሳዩ ካሉት የክልሉ አካባቢዎች መካከል ባሕርዳር ከተማ ይጠቀሳል። ጉዳዩን አስመልክቶ ኢዜአ ከባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ጌትነት አናጋው ጋር ቆይታ አድርጓል። ኃላፊ እንደገለጹት፥ ሕብረተሰቡ ከፀጥታ አካሉና ከአመራሩ ጋር ተቀራርቦ፣ ተናቦና ተቀናጅቶ በመስራቱ ከተማዋ ወደ ቀደመ ሰላሟ እንድትመለስ አስችሏል። ቀደም ሲል የፅንፈኛው ተላላኪዎች ዘረፋ፣ ስርቆትና እገታ በመፈፀም ሕዝቡን ለችግር ሲያጋልጡ እንደቆዩ አውስተዋል። ከከተማው ማሕበረሰብ ጋር በመተባበር በተከናወነው ቅንጅታዊ ስራ አጥፊዎችን በመለየት የሕግ የበላይነት ተከብሮ በከተማው ሰላም ማስፈን መቻሉን ገልጸዋል። አመራሩና የፀጥታ መዋቅሩ ከወጣቶች፣ሴቶች፣ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከሃይማኖት አባቶችና ከሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀትና በማወያየት ሰላም የፀና እንዲሆን ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ከሕዝቡ ጋር ተቀናጅተን በመስራታችን በከተማዋ የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት፣የኮንክሪት አስፓልት መንገድ ግንባታና ሌሎች የልማት ተግባራትን በማከናወን ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ሲሉም ተናግረዋል። በቀጣይም በከተማዋ የሰፈነውን አስተማማኝ ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል ከማሕብረተሰቡ ጋር የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ይበልጥ ጎልብቶ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በየአካባቢው የተቋቋሙ የማሕበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ማዕከላትን በማጠናከር፣ የሰላም አስከባሪና የሚሊሻ ኃይሉን አቅም በመገንባትና በሎጂስቲክስ በመደገፍ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይሰራል ሲሉ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ እየጸናች ትቀጥላለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 20, 2025 216
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ያለ ጥርጥር በትውልድ ቅብብሎሽ ፀንታ ትቀጥላለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በ‘የሶፍ ኡመር ወግ’ ከቀድሞ እና በሥራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያውያን ይሄን ሁሉ ጸጋ እና ሀብት ይዘን መለመናችን እጅጉን የሚያስቆጭ እና ልንቀይረው የሚገባ ጉዳይ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ታሪክ ቀይራ እንድትበለጽግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ያለ ጥርጥር ትውልድ ተቀባብሎ የሚያጸናት ሀገር ትሆናለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ጉዳዮች መልክ እየያዙ ይመጣሉ ሲሉም ገልጸዋል። ብልጽግናን ለማረጋገጥ ሁሉም በየአካባቢው ያለውን ሀብት እያወጣ ማልማት እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የሚበጀን በመደማመጥ፣ በመከባበር፣ በመተጋገዝ እና ተካፍሎ በጋራ መኖር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትብብር መንፈስ ከሰራን የምንመኘውን ሰላምና ብልጽግና ማምጣት እንችላለን ብለዋል።
የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ሁሉም ኢትዮጵያዊ አበክሮ ሊሰራ ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 20, 2025 145
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018(ኢዜአ):- የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ትጋት፣ ልፋት እና ድካም የሚጠይቅ ጉዳይ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በ‘የሶፍ ኡመር ወግ’ ከቀድሞ እና በሥራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀገር በአንድ ትውልድ አይሰራም አንድ ትውልድ ጀምሮ የሚጨርሰው ጉዳይ አይደለም ብለዋል። በየትኛውም ዓለም ያለ ሀገር የሚሰራው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትውልዶች የትናንት ማንነታቸው፣ የዛሬ መኖራቸው እና የነገ መጻኢ ጊዜ የጋራ ውጤቶች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል። የትውልድን የተሟላ ማንነት በውል መረዳት ሀገር የመገንባት ብቃት እና እሳቤን እንደሚያሰፋም ነው የተናገሩት። በዚህ የትውልድ ቅብብሎሽ ውስጥ ሀገር ትገነባለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁሉም በሚኖርበት ዘመን ውስጥ ለሀገሩ መልካም ከመመኘት ባለፈ መልፋት፣ መድከም እና መስራት እንዳለበት አመልክተዋል። ያለ ድካም እና ልፋት ሰላም እና ብልጽግና አይመጣም፤ ፍሬም ሊታይ አይችልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ሁሉም ኢትዮጵያዊ የምናልመውን ብልጽግና ለማምጣት በላቀ ትጋት ሊሰራ እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት።
በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚካሄዱ መድረኮችን በብቃት ማስተናገድ የሚያስችል የተቀናጀ አቅም ተገንብቷል
Oct 20, 2025 140
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 10/2018(ኢዜአ)፡- በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚካሄዱ መድረኮችን በብቃት ማስተናገድ የሚያስችል የተቀናጀ አቅም መገንባቱን የአማራ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሚካሄደው 11ኛው ጣና ፎረም የተደረገውን ዝግጅት በተመለከተ የጸጥታ አካላት የውይይት መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር)፤ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚካሄዱ መድረኮችን በብቃት ማስተናገድ የሚያስችል የተቀናጀ አቅም መገንባቱን ገልጸዋል። የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የጸጥታ ሃይሉ የላቀ ሚና እንዳለ ሆኖ የህዝቡ ትብብርና ጥረት ከፍተኛ አቅም መሆኑን አንስተዋል። በክልሉ ባህር ዳርን ጨምሮ የተለያዩ ከተሞች አስተማማኝ ሰላም መኖሩን አረጋግጠው በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም መሰረት ከቀናት በኋላ ለሚካሄደው ጣና ፎረም በሁሉም ረገድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን የቢሮው ኃላፊ አረጋግጠዋል። የጣና ፎረምን የኢትዮጵያን ከፍታ ብሎም የክልሉን ገፅታ በሚያሳይ መልኩ ተቀብሎ በማስተናገድ መልካም እሴቶችንና እንግዳ ተቀባይነትን ማሳየት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር)፤ የፖሊስ ተቋሙን መልሶ በማደራጀት ባለፉት ወራት በርካታ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። ለጣና ፎረም የተሟላና የተቀናጀ ዝግጅት መደረጉን ገልጸው ለፎረሙ ስኬታማነት የፀጥታ ኃይሉ አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት በማድረግ ወደ ስራ መግባቱን አረጋግጠዋል። በመድረኩ በፀጥታ ግብረ ሃይሉ የተካተቱ የክልሉና የፌደራል የፀጥታ አካላትና በየደረጃው ያሉ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
በህዝብ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ እንዲያገኙ ድጋፍ እና ቁጥጥር ይጠናከራል
Oct 20, 2025 199
አሶሳ፤ ጥቅምት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህዝቡ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ እንዲያገኙ ድጋፍ እና ቁጥጥር ይጠናከራል ሲሉ የክልሉ ምክርቤት አፈ-ጉባኤ አስካለች አልቦሮ ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የክልሉ ተመራጮች በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች ያከናወኑትን የህዝብ የውይይት መድረክ አስመልክቶ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ምክክር አድርገዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አስካለች አልቦሮ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ እና ሌሎች ትልልቅ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ውይይት መደረጉን ጠቅሰዋል። ክልሉ በራሱ አቅም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶችን እያከናወነ መሆኑን ተናግረው ለስኬታማነቱም ምክር ቤቶች ሚናቸውን ያጠናክራሉ ብለዋል። የተቋማት ተደራሽነት እና የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን በህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እንዲመለሱ ድጋፍ እና ቁጥጥሩ የሚጠናከር መሆኑንም ገልጸዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና የክልሉ ተመራጭ አቶ ሙባረክ ኤሊያስ በበኩላቸው፤ በክልሉ የሰፈነው ሠላም የተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲከናወኑ ማድረጉን በመስክ ምልከታ ማረጋገጣቸውን ጠቁመዋል። በህብረተሰቡ በተደጋጋሚ የሚነሳው የትራንስፖርት ችግር እና ሌሎች ተያያዠ ጉዳዮች እልባት እንዲያገኙ ቁጥጥር እና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
ለጣና ፎረም በሁሉም ረገድ የተሟላ ዝግጅት ተደርጓል
Oct 20, 2025 169
ባሕርዳር፤ ጥቅምት10/2018(ኢዜአ)፡- ከቀናት በኋላ ለሚካሄደው ጣና ፎረም በሁሉም ረገድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሚካሄደው 11ኛው ጣና ፎረም የተደረገውን ዝግጅት በተመለከተ የጸጥታ አካላት የውይይት መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተካሄዷል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ክንዱ ወንዴ፤ ከቀናት በኋላ ለሚካሄደው የጣና ፎረም በሁሉም ረገድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። በፎረሙ የሚታደሙ እንግዶች ሁሉ ከጉባኤው ተሳትፎም ባለፈ በሚኖራቸው ቆይታ በመልካም መስተንግዶና ጥሩ አቀባበል የማይረሳ ጊዜ እንዲያሳልፉ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ለዚህም የጸጥታ ሃይሉ ሰላምና ደህንነታቸውን በማስጠበቅ፤ የከተማውና የአካባቢው ህዝብ ደግሞ መልካም መስተንግዶ ማድረግ እድሚጠበቅበትም አስታውቀዋል። በጣና ፎረም ላይ ከተለያዩ አገራት የሚመጡትን ጨምሮ በርካታ ታዳሚዎች የሚገኙ በመሆኑ ከጸጥታም ይሁን ከቀአባበልና መስተንግዶ አንፃር ግብረ ሃይል ተቋቁሞ መሰራቱንና ዝግጅቱም መጠናቀቁን ተናግረዋል። የጣና ፎረም ለኢትዮጵያ ገጽታ ግንባታ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን አንስተው ጉባኤው የሚካሄድባት ባህር ዳር ከተማ ደግሞ የሰላም ተምሳሌትና የቱሪዝም መስህብነቷን የምታሳይበት መልካም አካጣሚ መሆኑንም አስረድተዋል። ፎረሙ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ምክክር የሚደረግበት መርሃ ግብር ያካተተ፤ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞችም የሚወያዩበት መሆኑ መገለጹ ይታወቃል። በርካታ ተሳታፊዎች እንደሚሳተፉበት የሚጠበቀው 11ኛው የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥቅምት 14 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በባሕዳር እና በአዲስ አበባ የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል።
ፖለቲካ
በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Oct 21, 2025 60
ሆሳዕና ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ) :- በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቷ የሚስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ኮሚሽኑ ከዝግጅት ምዕራፍ በመጀመር በሁሉም አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አሁን ላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ እያካሄደ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ሂደት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ሁሉን አቀፍና አካታች የውይይት ሂደትን አጠናክሮ የቀጠለ መሆኑንም ማረጋገጥ ይቻላል። ከዚህ አንፃር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የምክክር ሂደቱ የሀገርን ችግር በባለቤትነት በመያዝ በምክክር መፍታት የምንችልበት ታሪካዊ አጋጣሚ ላይ እንገኛለን ብለዋል። የኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች በውይይት ለመፍታት በሚደረገው ታሪካዊ አጋጣሚ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ አረጋግጠዋል። በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የቁጥጥር መምሪያ ኃላፊና የሆሳዕና ደብረ መዊዕ ገዳም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቢ ትፍስኢት ቀሲስ ዳዊት አብርሃም፤ ለችግሮች ሁሉ መፍቻ መንገድ ከውይይት የበለጠ አዋጭና አትራፊ መንገድ የለም ይላሉ። በመሆኑም የሀገርን ችግሮች ተመካክሮ በመፍታት ለትውልዱ ሁሉ የተመቸችና ሰላም የሰፈነባት ሀገር ማጽናት የጋራ አደራና ሃላፊነታችን ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስትና ዜጎች ያለችግር የሚኖሩባት ሀገር ለመገንባት ያለ ልዩነት ለምክክር መሰባሰብ አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የአብሮነትንና የሰላም እሴቶችን ማጠናከር እንዲሁም ሰላምን ማስተማር የኃይማኖት አባቶች ዋነኛ ተልዕኮ መሆኑን አንስተው ለምክክሩ መሳካት የላቀ ሚናችንን ለመወጣት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የወጣቶች ተወካይ እስማኤል ሻሜቦ፤ በበኩሉ በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት እየሰራን እንገኛለን ይህንኑም አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ኮሚሽኑ የጀመራቸውን ስራዎች በማገዝ ረገድ በተለይም ቤተ እምነቶች ከፍተኛ ሃላፊነት ያለባቸው በመሆኑ በዚሁ ልክ ለማገዝ ተዘጋጅተናል ሲልም አረጋግጧል። የቡታጅራ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ላቀች ወሰኔ፤ በሀገር ጉዳይ ላይ ተቀራርበን በመወያየት ችግሮችን መፍታት ባለመቻላችን ብዙ ዋጋ ያስከፈለን በመሆኑ አሁን ላይ ሁላችንም ለምክክር ዝግጁ መሆን አለብን ብለዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ለሀገር ሰላም፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነትና ለልማት እቅዶች ስኬት በጋራ መትጋት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል። "እኛ ኢትዮጵያውያን በአብሮነት በመጓዝ ወደ ተሻለ ምዕራፍ እንድንደርስ የውስጥ ችግሮቻችንን በመነጋገርና በመወያየት የመፍታት ባህላችንን ማዳበር አለብን" ያሉት የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ምህረት ተስፋዬ ናቸው፡፡ የጠመንጃ ትግል ኪሳራ እንጂ ትርፍ የሌለው በመሆኑ የሰላምን አማራጭ ብቻ በመከተል በምክክር ለችግሮች መፍትሄ ይዘን መቅረብ ይጠበቅብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን "የሴቶች፣ የወጣቶችና የአካል ጉዳተኞች ሚናና አስተዋጽኦ ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር " በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ክልሎች የውይይት መድረኮች በመካሄድ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት በሁሉም መስኮች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ ናቸው
Oct 21, 2025 128
ጎንደር ፤ ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ)፡ በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት በሁሉም መስኮች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ መሆናቸውን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የጎንደር ከተማ አስተዳደር የበጀት ዓመቱ ሶሰት ወራት የፓርቲ እና የመንግሥት የስራ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ እና የአማራ ክልል የከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)፤ በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት በሁሉም መስኮች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከዚህ አንፃር በጎንደር ከተማ የተከናወኑ የመሰረተ ልማትና የፕሮጀክቶች ግንባታዎች ጥሩ አፈፃፀም የታየባቸው መሆኑን አንስተው የመንግሥት ተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ ምቹ እና የተቀላጠፈ በማድረግ የህዝብን እንግልት ለማስቀረት የተከናወኑ ተግባራትም የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በጎንደር ከተማም እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ፈጠራን፣ የፍጥነትን፣ ጥራትና አዲስ የስራ ባህል ለውጥን በማምጣት አበረታች ውጤት የታየባቸው መሆናቸውን ገልጸዋል። በኮሪደር ልማት፣ በቅርስ ጥገናና እድሳት፣ በስራ እድል ፈጠራና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የተመዘገቡት ውጤቶች ሰላምን በጋራ በማረጋገጥ የመጣ ውጤት መሆኑን አስረድተዋል። እንደ አጠቃላይ የክልሉ መንግስት የቀጣይ 25 ዓመት አሻጋሪ የልማት እቅድ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀቱንም ዶክተር አሕመዲን ጠቁመዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው፤ በከተማ አስተዳደሩ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ሰላምን በማስጠበቅ የተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች በውጤት የተለኩና የህዝቡንም እርካታ በተጨባጭ ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። የዛሬ መድረክም የተሳኩ እቅዶችን የምናጠናክርበት፣ ደካማ አፈጻጸሞችን የምናርምበትና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ መግባባት በመፍጠር የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የምንተጋበት ነው ሲሉ ገልጸዋል። በመድረኩ የክልሉና በየደረጃው የሚገኙ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በባሕርዳር ከተማ ከሕብረተሰቡ ጋር የተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን አስችሏል
Oct 21, 2025 99
ባሕርዳር፤ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ) ፡-በባሕርዳር ሕብረተሰቡን በማስተባበር የተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር በከተማዋ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ማስቻሉን የከተማው አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ። በአማራ ክልል በየደረጃው ሲካሄዱ በቆዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሕብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ሰላምን ለማጽናት ያለውን የፀና አቋም በተግባር እያሳየ ነው። ይህንን በቁርጠኝነት በተግባር እያሳዩ ካሉት የክልሉ አካባቢዎች መካከል ባሕርዳር ከተማ ይጠቀሳል። ጉዳዩን አስመልክቶ ኢዜአ ከባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ጌትነት አናጋው ጋር ቆይታ አድርጓል። ኃላፊ እንደገለጹት፥ ሕብረተሰቡ ከፀጥታ አካሉና ከአመራሩ ጋር ተቀራርቦ፣ ተናቦና ተቀናጅቶ በመስራቱ ከተማዋ ወደ ቀደመ ሰላሟ እንድትመለስ አስችሏል። ቀደም ሲል የፅንፈኛው ተላላኪዎች ዘረፋ፣ ስርቆትና እገታ በመፈፀም ሕዝቡን ለችግር ሲያጋልጡ እንደቆዩ አውስተዋል። ከከተማው ማሕበረሰብ ጋር በመተባበር በተከናወነው ቅንጅታዊ ስራ አጥፊዎችን በመለየት የሕግ የበላይነት ተከብሮ በከተማው ሰላም ማስፈን መቻሉን ገልጸዋል። አመራሩና የፀጥታ መዋቅሩ ከወጣቶች፣ሴቶች፣ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከሃይማኖት አባቶችና ከሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀትና በማወያየት ሰላም የፀና እንዲሆን ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ከሕዝቡ ጋር ተቀናጅተን በመስራታችን በከተማዋ የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት፣የኮንክሪት አስፓልት መንገድ ግንባታና ሌሎች የልማት ተግባራትን በማከናወን ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ሲሉም ተናግረዋል። በቀጣይም በከተማዋ የሰፈነውን አስተማማኝ ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል ከማሕብረተሰቡ ጋር የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ይበልጥ ጎልብቶ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በየአካባቢው የተቋቋሙ የማሕበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ማዕከላትን በማጠናከር፣ የሰላም አስከባሪና የሚሊሻ ኃይሉን አቅም በመገንባትና በሎጂስቲክስ በመደገፍ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይሰራል ሲሉ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ እየጸናች ትቀጥላለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 20, 2025 216
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ያለ ጥርጥር በትውልድ ቅብብሎሽ ፀንታ ትቀጥላለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በ‘የሶፍ ኡመር ወግ’ ከቀድሞ እና በሥራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያውያን ይሄን ሁሉ ጸጋ እና ሀብት ይዘን መለመናችን እጅጉን የሚያስቆጭ እና ልንቀይረው የሚገባ ጉዳይ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ታሪክ ቀይራ እንድትበለጽግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ያለ ጥርጥር ትውልድ ተቀባብሎ የሚያጸናት ሀገር ትሆናለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ጉዳዮች መልክ እየያዙ ይመጣሉ ሲሉም ገልጸዋል። ብልጽግናን ለማረጋገጥ ሁሉም በየአካባቢው ያለውን ሀብት እያወጣ ማልማት እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የሚበጀን በመደማመጥ፣ በመከባበር፣ በመተጋገዝ እና ተካፍሎ በጋራ መኖር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትብብር መንፈስ ከሰራን የምንመኘውን ሰላምና ብልጽግና ማምጣት እንችላለን ብለዋል።
የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ሁሉም ኢትዮጵያዊ አበክሮ ሊሰራ ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 20, 2025 145
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018(ኢዜአ):- የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ትጋት፣ ልፋት እና ድካም የሚጠይቅ ጉዳይ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በ‘የሶፍ ኡመር ወግ’ ከቀድሞ እና በሥራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀገር በአንድ ትውልድ አይሰራም አንድ ትውልድ ጀምሮ የሚጨርሰው ጉዳይ አይደለም ብለዋል። በየትኛውም ዓለም ያለ ሀገር የሚሰራው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትውልዶች የትናንት ማንነታቸው፣ የዛሬ መኖራቸው እና የነገ መጻኢ ጊዜ የጋራ ውጤቶች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል። የትውልድን የተሟላ ማንነት በውል መረዳት ሀገር የመገንባት ብቃት እና እሳቤን እንደሚያሰፋም ነው የተናገሩት። በዚህ የትውልድ ቅብብሎሽ ውስጥ ሀገር ትገነባለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁሉም በሚኖርበት ዘመን ውስጥ ለሀገሩ መልካም ከመመኘት ባለፈ መልፋት፣ መድከም እና መስራት እንዳለበት አመልክተዋል። ያለ ድካም እና ልፋት ሰላም እና ብልጽግና አይመጣም፤ ፍሬም ሊታይ አይችልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ሁሉም ኢትዮጵያዊ የምናልመውን ብልጽግና ለማምጣት በላቀ ትጋት ሊሰራ እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት።
በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚካሄዱ መድረኮችን በብቃት ማስተናገድ የሚያስችል የተቀናጀ አቅም ተገንብቷል
Oct 20, 2025 140
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 10/2018(ኢዜአ)፡- በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚካሄዱ መድረኮችን በብቃት ማስተናገድ የሚያስችል የተቀናጀ አቅም መገንባቱን የአማራ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሚካሄደው 11ኛው ጣና ፎረም የተደረገውን ዝግጅት በተመለከተ የጸጥታ አካላት የውይይት መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር)፤ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚካሄዱ መድረኮችን በብቃት ማስተናገድ የሚያስችል የተቀናጀ አቅም መገንባቱን ገልጸዋል። የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የጸጥታ ሃይሉ የላቀ ሚና እንዳለ ሆኖ የህዝቡ ትብብርና ጥረት ከፍተኛ አቅም መሆኑን አንስተዋል። በክልሉ ባህር ዳርን ጨምሮ የተለያዩ ከተሞች አስተማማኝ ሰላም መኖሩን አረጋግጠው በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም መሰረት ከቀናት በኋላ ለሚካሄደው ጣና ፎረም በሁሉም ረገድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን የቢሮው ኃላፊ አረጋግጠዋል። የጣና ፎረምን የኢትዮጵያን ከፍታ ብሎም የክልሉን ገፅታ በሚያሳይ መልኩ ተቀብሎ በማስተናገድ መልካም እሴቶችንና እንግዳ ተቀባይነትን ማሳየት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር)፤ የፖሊስ ተቋሙን መልሶ በማደራጀት ባለፉት ወራት በርካታ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። ለጣና ፎረም የተሟላና የተቀናጀ ዝግጅት መደረጉን ገልጸው ለፎረሙ ስኬታማነት የፀጥታ ኃይሉ አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት በማድረግ ወደ ስራ መግባቱን አረጋግጠዋል። በመድረኩ በፀጥታ ግብረ ሃይሉ የተካተቱ የክልሉና የፌደራል የፀጥታ አካላትና በየደረጃው ያሉ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
በህዝብ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ እንዲያገኙ ድጋፍ እና ቁጥጥር ይጠናከራል
Oct 20, 2025 199
አሶሳ፤ ጥቅምት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህዝቡ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ እንዲያገኙ ድጋፍ እና ቁጥጥር ይጠናከራል ሲሉ የክልሉ ምክርቤት አፈ-ጉባኤ አስካለች አልቦሮ ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የክልሉ ተመራጮች በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች ያከናወኑትን የህዝብ የውይይት መድረክ አስመልክቶ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ምክክር አድርገዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አስካለች አልቦሮ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ እና ሌሎች ትልልቅ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ውይይት መደረጉን ጠቅሰዋል። ክልሉ በራሱ አቅም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶችን እያከናወነ መሆኑን ተናግረው ለስኬታማነቱም ምክር ቤቶች ሚናቸውን ያጠናክራሉ ብለዋል። የተቋማት ተደራሽነት እና የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን በህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እንዲመለሱ ድጋፍ እና ቁጥጥሩ የሚጠናከር መሆኑንም ገልጸዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና የክልሉ ተመራጭ አቶ ሙባረክ ኤሊያስ በበኩላቸው፤ በክልሉ የሰፈነው ሠላም የተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲከናወኑ ማድረጉን በመስክ ምልከታ ማረጋገጣቸውን ጠቁመዋል። በህብረተሰቡ በተደጋጋሚ የሚነሳው የትራንስፖርት ችግር እና ሌሎች ተያያዠ ጉዳዮች እልባት እንዲያገኙ ቁጥጥር እና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
ለጣና ፎረም በሁሉም ረገድ የተሟላ ዝግጅት ተደርጓል
Oct 20, 2025 169
ባሕርዳር፤ ጥቅምት10/2018(ኢዜአ)፡- ከቀናት በኋላ ለሚካሄደው ጣና ፎረም በሁሉም ረገድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሚካሄደው 11ኛው ጣና ፎረም የተደረገውን ዝግጅት በተመለከተ የጸጥታ አካላት የውይይት መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተካሄዷል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ክንዱ ወንዴ፤ ከቀናት በኋላ ለሚካሄደው የጣና ፎረም በሁሉም ረገድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። በፎረሙ የሚታደሙ እንግዶች ሁሉ ከጉባኤው ተሳትፎም ባለፈ በሚኖራቸው ቆይታ በመልካም መስተንግዶና ጥሩ አቀባበል የማይረሳ ጊዜ እንዲያሳልፉ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ለዚህም የጸጥታ ሃይሉ ሰላምና ደህንነታቸውን በማስጠበቅ፤ የከተማውና የአካባቢው ህዝብ ደግሞ መልካም መስተንግዶ ማድረግ እድሚጠበቅበትም አስታውቀዋል። በጣና ፎረም ላይ ከተለያዩ አገራት የሚመጡትን ጨምሮ በርካታ ታዳሚዎች የሚገኙ በመሆኑ ከጸጥታም ይሁን ከቀአባበልና መስተንግዶ አንፃር ግብረ ሃይል ተቋቁሞ መሰራቱንና ዝግጅቱም መጠናቀቁን ተናግረዋል። የጣና ፎረም ለኢትዮጵያ ገጽታ ግንባታ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን አንስተው ጉባኤው የሚካሄድባት ባህር ዳር ከተማ ደግሞ የሰላም ተምሳሌትና የቱሪዝም መስህብነቷን የምታሳይበት መልካም አካጣሚ መሆኑንም አስረድተዋል። ፎረሙ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ምክክር የሚደረግበት መርሃ ግብር ያካተተ፤ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞችም የሚወያዩበት መሆኑ መገለጹ ይታወቃል። በርካታ ተሳታፊዎች እንደሚሳተፉበት የሚጠበቀው 11ኛው የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥቅምት 14 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በባሕዳር እና በአዲስ አበባ የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል።
ማህበራዊ
በክልሉ በስርዓተ ፆታ አካታችነት በማጠናከር የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ ነው
Oct 21, 2025 25
አዳማ፤ ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ የስርዓተ ፆታ አካታችነት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ገለፀ። ቢሮው በክልሉ በስርዓተ ፆታ እኩልነት አተገባበርና በታዩ ውስንነቶች ላይ ከኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርስቲና ከክልሉ የስራ ዕድል ፈጠራ ቢሮ ጋር በመተባበር ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የምክክር መድረክ በአዳማ አካሄዷል። የኦሮሚያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በክልሉ የስርዓተ ፆታ እኩልነትን ከማረጋገጥ አንጻር የሚታዩ ውስንነቶችን ለመፍታት ትኩረት ተደርጓል። በተለይ በክልሉ የመንግሥት መዋቅሮች የስርዓተ ፆታ እኩልነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም የህፃናትን መብትና ደህንነት የማስጠበቅ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በዚህም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ማነቆ የሆኑ ችግሮች እየተፈቱ መሆኑንም ተናግረዋል። ሴቶች ከኢኮኖሚ ጥገኝነት እንዲላቀቁና ራሳቸውን እንዲችሉ በግብርና፣ በአገልግሎትና በተለያዩ የስራ መስኮች ተሳትፏቸው እንዲጎለብት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በበጎ ፈቃድ አገልግሎትም ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል። የዛሬው መድረክም በክልሉ መንግሰት መዋቅር ውስጥ በስርዓተ ፆታ እኩልነትና ተግባራዊነት ላይ የተገኙ ውጤታማ ተሞክሮዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና የተለዩ ክፍተቶችን ለመሙላት በጋራ ዕቅድ የተደገፈ የተቀናጀ ርብርብ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል። በጨፌ ኦሮሚያ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ መስታወት ፈይሳ፣ የምክር ቤት አባላቱ በዕቅድና በመስክ ምልክታ የሴቶችን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንፃር አበረታች ስራዎች እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ ከዕቅድ ጀምሮ ከወረዳ እስከ ክልሉ የመንግስት መዋቅር ድረስ በየደረጃው ባለው ተቋማት የስርዓተ ፆታ እኩልነት ትግበራ ላይ ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል። ''የስርዓተ ፆታን ተግባራዊነት ከማረጋገጥ አንፃር ከተቋም ተቋም ልዩነት ቢኖርም መሻሻል አለ'' ያሉት ሰብሳቢዋ በተለይ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ከማረጋገጥና ሴቶች ወደ ውሳኔ ሰጪነት እንዲመጡ ከማድረግ አንፃር አበረታች ውጤት እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ በስራ ዕድል ፈጠራና ሴቶች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ በተቀናጀ መልኩ መሰራት እንዳለበትም አመለክተዋል። የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርስቲ ተመራማሪ አቶ ሀብታሙ ደሳለኝ በበኩላቸው የስርዓተ ፆታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ እና በዕቅድ የሚመራ ስራ ማከናወን ያስፈልጋል ብለዋል። በስርዓተ ፆታ ተግባራት ዙሪያ ያለው ግንዛቤ በሁሉም መልኩ ማደጉ፣ የሴቶች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ውሳኔ ሰጪነት ሚና እያደገ መምጣቱ አበረታች ጥረት መሆኑን አስረድተዋል። በዩኒቨርስቲው አማካኝነት በስርዓተ ፆታ እኩልነትና ተግባራዊነት ላይ አተኩሮ ጥናት መካሄዱን ገልጸው በጥናቱ መሰረትም መሻሻሎች ቢኖሩም በርካታ ስራዎች ይቀራሉ ብለዋል።
በምስራቅ ወለጋ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎ የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከል ጥረት እየተደረገ ነው
Oct 21, 2025 49
ነቀምቴ፤ ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የወባ በሽታን ስርጭትን በህብረተሰብ ተሳትፎ ለመከላከል ጥረት እየተደረገ መሆኑን የምስራቅ ወለጋ ዞን ጤና ፅህፈት ቤት ገለጸ። የምስራቅ ወለጋ ዞን ጤና ፅህፈት ቤት ሀላፊ ቡልቶሳ ቡሻ እንደገለጹት የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከል የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግና የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን ማፅዳት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል። በእስካሁኑ ጥረትም የክረምት ወቅት መውጣቱን ተከትሎ የሚከሰትን የወባ ስርጭት ለመቆጣጠር ህብረተሰቡን ያሳተፈ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል። የወባ በሽታ ስርጭትን የመከላከል ስራውን ውጤታማ ለማድረግ በመረጃ ላይ የተመሰረተ የምርመራና የህክምና አገልግሎትን እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። የጤና ባለሙያዎች የቤት ለቤት ክትትል በማድረግ ህብረተሰቡ ጤናውን እንዲጠብቅ ግንዛቤ እየሰጡ ሲሆን 682 ሺህ 540 የአልጋ አጎበር መስራጨቱንና የኬሚካል ርጭት መካሄዱን አንስተዋል። የነቀምቴ ከተማ ሶርጋ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሰኚ ሺፈራ፣ የወባ ወረርሽኝን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ከሌሎች ነዋሪዎች ጋር በመተባበር ውሀ ያቆሩ አካባቢዎችን ማፋሰሳቸውን ተናግረዋል። የጤና ባለሞያዎች በሚስተምሩዋቸው መሰረት የአልጋ አጎበሮችን በአግባቡ እየተጠቀሙ መሆኑን ገልጸው ወደ ፊትም የወባ በሽታ ምልክት ሲያጋጥማችው ፈጥነው ወደ ህክምና ተቋም እንደሚሄዱም ተናግረዋል። የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ምትኩ ግርማ በበኩላቸው በሽታውን ለመከላከልም የአካባቢ ጽዳት ላይ መስራታቸውን አመልክተዋል።
ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ ነው
Oct 21, 2025 87
ሮቤ፣ ጥቅምት11/2018(ኢዜአ) ፡-መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ብርሃነ መስቀል ጠና (ዶ/ር) ተናገሩ። መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በስፔን አገር ከሚገኘው ሰርጀሪ ሶሊዳሪቲ ከተባለ ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት አድርጓል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነ መስቀል ጠና (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ለመወጣት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ ነው። ዩኒቨርሲቲው በተለይ በጤና፣ በግብርና፣ በተፈጥሮ ሀብት፣ በቱሪዝምና በሌሎች ዘርፎች ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ እየሰራ መሆኑን አመልክቷል። በተለይም በስሩ በሚገኘው የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል የአካባቢው ማህበረሰብ የተሻለ የጤና አገልግሎት ማግኘት እንዲችል የተለያየ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ከ”ሰርጀሪ ሶሊዳሪቲ” ድርጅት ጋር የተደረገው ስምምነትም በሆስፒታሉ እየተሰጠ የሚገኘውን የእንቅርት (ጎይተር) የቀዶ ህክምና አገልግሎትን በቴክኖሎጂ እንዲታገዝና ይበልጥ እንዲዘምን ዕድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ በጎባ ሪፈራል ሆስፒታል የዘርፉ የህክምና ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ልምድ እንዲያገኙና የተሻለ የህክምናና የምርምር ስራዎችን በስፋት ለማካሄድ እንደሚረዳ ተናግረዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል የእንቅርት የቀዶ ህክምና ማሻሻያ ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶክተር ከበበ በቀለ በበኩላቸው የተደረገው ስምምነት የእንቅርት ታማሚዎች የቀዶ ህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገር የእውቀት ሽግግር ለማድረግ ያግዛል ብለዋል። የድርጅቱ የሐኪሞች ቡድን በመጀመሪያ ቀን ውሎው ለአምስት የበሽታው ታካሚዎች የተሳካ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ማድረጉንም አመልክተዋል። በሚቀጥሉት አራት ቀናት በሆስፒታሉ ቀድመው የተለዩ ሌሎች 25 ታካሚዎች የህክምና አገልግሎት ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል። የ”ሰርጀሪ ሶሊዳሪቲ” ድርጅት ሊቀመንበር ዶክተር ጆሴ ማኑኤል በበኩላቸው፤ በሁለቱ ተቋማት መካከል የተደረገው የመግባቢያ ስምምነት በተለይ በእንቅርት የቀዶ ህክምና ዘርፍ የእውቀት ሽግግር ለማድረግ ዕድልን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ የፍትህ መጓተትን በማስቀረት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል
Oct 21, 2025 79
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ):-የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ የፍትህ መጓተትን በማስቀረት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል ሲሉ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ኪያር ገለጹ። የጉዳዮች ፍሰት አስተዳዳር የዳኝነት አገልግሎት ቀልጣፋ፣ ተገማችና ተገልጋይ እርካታ የሚያገኝበት እንዲሆን ከማድረጉ ባሻገር የአገልግሎት ጥራትን ለማሳደግና፤ የመዝገብ ክምችትን ለመቀነስ ጉልህ ድርሻ አለው፡፡ የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር የጉዳዮች መቋጫና እልባት መስጫ ጊዜ መጓተት የሚያስከትለውን ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ መቀነስ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት ወሳኝ መሆኑን ባለሙያዎች ይገልጻሉ፡፡ እንዲሁም የዳኝነት ነፃነት፣ ተጠያቂነትና ሚዛናዊነት ተጠብቆ ዜጎች በአጭር ጊዜ ጥራት ያለው የዳኝነት አገልግሎት እንዲያገኙና በዳኝነት ስርዓቱ ላይ ያላቸው አመኔታና እርካታ እያደገ እንዲሄድ የሚያስችል ነው፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ኪያር ለኢዜአ እንደገለጹት ከለውጡ በኋላ በፍትህ ዘርፉ የተደረጉ ዋና ዋና ሪፎርሞች ውጤት በማስገኘት ላይ ናቸው ። በተለይም ለፍትህ እጦት በምክንያትነት ሲጠቀስ የነበረውን የጉዳዮች መጓተት ለማስቀረት ከለውጡ በኋላ ከተወሰዱት መጠነ ሰፊ እርምጃዎች መካከል የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር ትልቅ ቦታ እንደሚሰጠው ገልጸዋል። ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በ2014 ዓ.ም. ያወጣው የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ የጉዳዮች መጓተትን ከመቅረፍ አንጻር ቁልፍ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ቀደም ሲል አንድ ጉዳይ የሚጀመርበትና የሚያልፍበት የጊዜ ገደብ እንደማይታወቅ አስታውሰው፣ አሁን ባለው መመሪያ ግን ለእያንዳንዱ ጉዳይ ግልጽ የጊዜ ገደብ ተቀምጦ እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት የጊዜ ገደብ ያለፈባቸው ፋይሎች ላይ የዘገየ የሚል ምልክት በመለጠፍና ለጉዳዩ ቅድሚያ በመስጠት የተቀላጠፈ ውሳኔ እንዲሰጥባቸው እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። ከዚህ ባለፈ ያለአግባብ ቀጠሮ በሚያዛቡ ዳኞች ላይ ተጠያቂነት የማስፈን ስራ መጀመሩን ጠቁመው፤ ይህም ዳኞች ጉዳዮችን በፍጥነት እንዲያዩ በማድረግ፣ የጉዳዮች መዘግየት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቀንስ አድርጓል ብለዋል። ከሪፎርሙ በኋላ በፍርድ ቤት አገልግሎት ተደራሽነትና በዳኝነት ነጻነት ላይ ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ፕሬዝዳንቱ አመልክተዋል። በፍትህ ስርዓቱ አሰራር ላይ ተግባራዊ መደረግ የጀመረው የቴክኖሎጂ ስራ መልካም አስተዳደርን ለማረጋገጥና ቀልጣፋ ውሳኔ ለመስጠት አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ፕሬዝዳንቱ ጨምረው ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
በደሴ ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የስራ መስኮች ላይ የተሰማሩ ሴቶች ውጤታማ መሆን ችለዋል
Oct 21, 2025 10
ደሴ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፡ - በደሴ ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የስራ መስኮች የተሰማሩ ሴቶች ውጤታማ መሆናቸውን ተናገሩ። የክልሉ፣ የዞንና የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴት አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በደሴ ከተማ በልማት ሕብረት በተደራጁ ሴቶች የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የሴቶቹ የስራ ዘርፎች የባልትና ውጤቶችና የሌማት ትሩፋት መርሃ ገብርን ጨምሮ ሌሎችም ይገኙበታል። በሴቶች የልማት ሕብረት ሶስት ሆነው በመደራጀት በባልትና ስራ ላይ ከተሰማሩት መካከል ወይዘሮ ዘሪቱ ጌታቸው፤ የተለያዩ የባልትና ውጤቶችን በማዘጋጀት ለገበያ በማቅረብ ትርፋማ መሆናቸውንና ለ30 ሴቶችም የሥራ እድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግረዋል። ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ አሊማ አስፋው የከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸላቸው መሬት የተለያዩ አትክልቶችን በማልማት ከቤት ፍጆታ አልፈው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። በወተት ላም እርባታ ላይ የተሰማሩት ወይዘሮ ወርቄ ከልካይም፤ በቀን ከ400 ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። በጥቂት ላሞች የጀመሩት ስራ አሁን ላይ ቁጥራቸው ጨምሮ 43 መድረሱን ጠቅሰው ፤ ስራውን አጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ምሳዬ ከድር፤ በሴቶች ልማት ሕብረት ከ71 ሺህ በላይ ሴቶች ተደራጅተው ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸው፤ በየተሰማሩባቸው ዘርፎችም ውጤታማ ሆነዋል ብለዋል። የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ዝና ጌታቸው በበኩላቸው፤ ሴቶችን በማደራጀት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ ረገድ የተጀመሩ ጥረቶች ውጤት እያታየባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትም ባለፈ በፖለቲካና ማህበራዊ ዘርፎችም ጠንካራ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ይሰራል ሲሉ አረጋግጠዋል።
ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ከአሜሪካ የግምጃ ቤት እና ስቴት ዲፓርትመንት የስራ ሀላፊዎች ጋር የኢኮኖሚ ትብብርን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መከሩ
Oct 21, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፦ በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ ከአሜሪካ የግምጃ ቤት እና ስቴት ዲፓርትመንት የስራ ሀላፊዎች ጋር የኢኮኖሚ ትብብርን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። ውይይቱ የተካሄደው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብሰባ ጎን ለጎን ነው። በውይይቱም አቶ አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያን ወቅታዊ የልማትና ዕድገት ሁኔታ እንዲሁም የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ሂደትን የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግስት ግልጸኝነትን ለማስፈን፣ የመንግስት አስተዳደርን ለማጠናከርና የቢዝነስና ኢንቨስትመንት ምህዳሩን የበለጠ ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅሞች በሆኑ ማለትም አሜሪካ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም የምታደርገውን ድጋፍ በተለይ በባለብዙ ወገን ባንኮችና በዓለም ገንዘብ ድርጅት በኩል እንዲሁም በንግድና ኢንቨስትመንት ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተመላክቷል። የአሜሪካ የስራ ሀላፊዎች በበኩላቸው አሜሪካ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤታማነት የቴክኒክ ድጋፍን ጨምሮ በግሉ ዘርፍ በመሳተፍ እና ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር በመተባበር የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። ሁለቱ ወገኖች ቀዳሚ በሆኑና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ በሚያስችሉ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮቻቸው ላይ የሚያደርጉትን ውይይት አጠናክሮ ለማስቀጠል ተስማምተዋል።
የሕዳሴ ግድብ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁሞ መጨረስ እንደሚቻል አሳይቷል፤ የቀድሞ ትርክትን ቀይሯል
Oct 21, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ጫናዎችን ተቋቁማ መፈጸም እንደምትችል ያሳየ፤ ዓባይ ግንድ ይዞ ይዞራል የሚለውን ትርክት የቀየረ ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ኮሚቴ እና አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም የጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አማረች በካሎ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ እንድትታይ አድርጓል፡፡ ለዘመናት ሲነገር የቆየው "ዓባይ ግንድ ይዞ ይዞራል" የሚለው ትርክት በአዲስ አስተሳሰብ በመቀየር የኢትዮጵያውያንን መቻል ገልጧል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን የትኛውም ዓለም አቀፍ ጫና ሳይበግራት መፈጸም እንደምትችል ማረጋገጫ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ሀብታችንን በፍትሐዊነት በመጠቀም ለቀጣናው ልማትና ትስስር በጋራ እንድምንሰራ ዳግም ያረጋገጥንበት ፕሮጀክታችንም ነው ብለዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጆ፤ የሕዳሴ ግድብ ህዝቡን በፈቃደኝነት ማነሳሳት ትልቅ የፋይናንስ አቅም መሆኑን አረጋግጧል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመላቀቅ በራሷ የበጀት አቅም ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረግ እንድምትችል ማስተማሪያ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በውጭ ብድር ቢጀመር ኖሮ ለዘመናት እንደቆመ ይቀራል እንጂ አይጠናቀቅም ነበር ብለዋል፡፡ በግንባታ ወቅት ሲደርሱ የቆዩት ዓለም አቀፍ ጫናዎች ትልቅ ማሳያዎች ናቸው ያሉት ሰብሳቢው፤ የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ አቅሟን ያሳየችበት ለነገ ልምድ የወሰደችበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምክር ቤቱ የውሃ፣ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች እና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፈቲያ አህመድ በበኩላቸው፤ የሕዳሴ ግድብ የመላ ኢትዮጵያውያን የላብ የደምና የእንባ ጠብታ ድምር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሕዳሴ የኢትዮጵያውያን አንድነትና ትብብር ማጠናከሪያ፣ የአይበገሬነት ማሳያ እና የቁርጠኝነታቸው ማረጋገጫ ነው ብለዋል፡፡ በሁሉም የዓለም ማዕዘን ያሉ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከአርሶ አደር እስከ አርብቶ አደር፣ ከነጋዴ እስከ መንግስት ሰራተኛ ያወጡት ገንዘብ ባክኖ እንዳልቀረ ማሳያ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ከሁሉም ኢትዮጵያውያን በተዋጣ ሀብት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እንደተጠናቀቀ ሁሉ ሌሎች ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ለመጨረስ መረባረብ ይገባናል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች የኢኮኖሚ እድገትን የሚያፋጥኑና ለአፍሪካውያን የመነሳት ምሳሌ ናቸው
Oct 21, 2025 76
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ):- በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ሜጋ የልማት ፕሮጀክቶች ኢኮኖሚያዊ እድገትን በማፋጠን የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ እና አፍሪካውያን በራሳቸው አቅም ግቦቻቸውን ለማሳካት የመነሳታቸው ማሳያ መሆናቸውን የምጣኔ ሀብት ምሁራን ገለጹ። በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር የሰው ሃብት ልማትና ድህነት ቅነሳ ከፍተኛ ተመራማሪው ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ሀገራት ተግባራዊ የሚያደርጓቸው የልማት ሥራዎች እንደየነባራዊ ሁኔታቸው ቢለያዩም ጥቅል ግባቸው ሀገርን ወደ ከፍታ ማሻገር ነው። በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት የዜጎቻቸውን ኑሮ የሚያሻሽሉና ኢኮኖሚያቸውን የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች ላይ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉና የተጠናቀቁ ሜጋ ፕሮጀክቶች በጥናት ላይ የተመሰረቱ፣ ዘላቂ ልማትን እና እድገትን በማሳካት የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋገጡ መሆናቸውን አብራርተዋል። ለኢንቨስትመንት ተጨማሪ አቅምን መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸው ለአካታች ኢኮኖሚ ግንባታ መጎልበት ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸውም ጠቁመዋል። የኢኮኖሚ ልማት ባለሙያና የፋይናንስ ጉዳይ አማካሪ አቶ ደረጀ ደጀኔ በበኩላቸው በኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ጀምሮ የመጨረስ ባህል እየዳበረ መጥቷል ብለዋል። የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች፣ የከተሞችን ዕድገት የሚያፋጥኑና የዜጎችን ኑሮ የሚያሻሽሉ በርካታ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸውንም በማሳያነት ጠቅሰዋል። የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ እድገት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች እየተጠናቀቁና እየተጀመሩ መሆናቸው ሀገራዊ ፋይዳቸው የላቀ መሆኑን አብራርተዋል። እነዚሁ ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢንቨስትመንት ተመራጭና ተወዳዳሪ እንድትሆን ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውንም ነው ያስረዱት። እንደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ያሉ ፕሮጀክቶች ደግሞ ለጎረቤት ሀገራት የኃይል አቅርቦትን ጨምሮ በመሰረተ ልማት የመተሳሰር እድልን የሚፈጥሩ በመሆናቸው ለጋራ ዕድገት ወሳኝ ሚና አላቸው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን ከማፋጠን ባለፈ አፍሪካውያን በራስ አቅም የትኛውንም የልማት ስራ በማከናወን ግቦቻቸውን ለማሳካት የመነሳታቸው ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የዩኒቨርሲቲ - ኢንዱስትሪ ትስስር የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግርን ያጎለብታል - ምሁራን
Oct 20, 2025 127
ሐረማያ፤ ጥቅምት 10/2018(ኢዜአ)፦ የዩኒቨርሲቲ - ኢንዱስትሪ ትስስር የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር እንዲጎለብት በማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ የሚያበረክት መሆኑን ምሁራን ገለጹ። የምስራቅ ኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር ፎረም ምስረታ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። በምክክሩ መድረክ ላይ የተሳተፉት ምሁራን ለኢዜአ እንደተናገሩት የዩኒቨርሲቲ - ኢንዱስትሪ ትስስር የምርምር ቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር እንዲጎለብት ፋይዳው የላቀ ነው። በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ትስስር አስተባባሪ ፈይሳ ሁንዴሳ እንዳሉት፤ ትስስሩ ከዚህ ቀደም ዩኒቨርሲቲዎችና - ኢንዱስትሪዎች በተበጣጠሰ መንገድ የሚያከናውኑት ስራዎችን ወጥ እንዲሆን የሚያስችል ነው። ትስስሩም የዩኒቨርsiቲ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የቀሰሙትን እውቀት በኢንዱስትሪዎች የተግባር ልምምድ እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል። ትስስሩ ኢንዱስትሪዎች የሚያጋጥማቸውን ችግሮች ለመፍታት ከዩኒቨርሲቲዎች ስልጠና፣ ማማከርና የምርምር ቴክኖሎጂ ውጤቶችን እንዲያገኙ ያስችላል ያሉት ደግሞ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የኢንዱስትሪ ትስስርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር እሸቱ መኮንን(ዶ/ር) ናቸው። በኦዳ ቡልቱ ዩኒቨርሲቲ የምርምር፣ ዓለም አቀፍ ግንኙነት እና አጋርነት ዳይሬክተር ጥምቀተ ዳኜ(ዶ/ር) በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲ - ኢንዱስትሪ ትስስር ሀገራዊ የልማት እቅዶችን በጋራ ለማሳካት እገዛ ያደርጋል። እንዲሁም የማህበረሰብ ችግሮችን በቅርበት ለመፍታትና የጋራ ችግሮችን አቅዶ በጋራ ለመቅረፍ ብሎም መፍትሄ ለማምጣት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አክለዋል። ትስስሩ ዩኒቨርሲቲዎችን ከኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር በተግባርና ንድፈ-ሃሳብ የዳበረ የሰው ሃይል ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ ነጻ ንግድ ቀጣና ዋና ስራ አስኪያጅ አህመድ ረሺድ ናቸው። በፎረም ምስረታው የምክክር መድረክ ላይ የሐረማያ፣ ድሬዳዋ፣ ሰመራ፣ ጅግጅጋ፣ ኦዳቡልቱምና ቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲዎች፣ የትምህርት ሞያ ስልጠና ኮሌጆች እንዲሁም በአካባቢው የሚገኙ የመንግስት እና የግል ኢንዱስትሪ ተወካዮች ተገኝተዋል።
ስታርት አፕ ለስራ እድል ፈጠራ እድገት የሚኖረውን አቅም ለመጠቀም ምቹ መደላድል እየተፈጠረ ነው
Oct 19, 2025 200
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፡-ስታርት አፕ ለስራ እድል ፈጠራ እድገት የሚኖረውን አቅም ለመጠቀም ምቹ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለፁ። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የስታርት አፕ ስነ ምኅዳሩን ማስፋት የሚያስችል የክህሎት ልማት እና አዳዲስ የስራ ዕድል ፈጠራን የሚያበረታቱ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ አዳዲስ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች የሚወዳደሩበት "ብሩህ ኢትዮጵያ" የክህሎት ውድድር ሀገራዊ ልማትን የሚያሳልጥና ስታርት አፖችን ማፍራት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ባለፉት አራት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 1 ሺህ 350 የፈጠራ ሀሳብ ላላቸው ዜጎች እውቅና ተሰጥቷል ብለዋል፡፡ በሀገሪቱ የሚኖረውን ፋይዳ አሟጦ ለመጠቀም አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብ ላላቸው ስታርት አፖች የመስሪያ ቦታ፣ የፋይናንስ፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡ የዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ስታርት አፕ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ ስታርት አፖች ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የስታርት አፕ ዘርፍ ኃላፊ ሙልጌታ ውቤ በበኩላቸው፤የወጣቶች የስራ ፈጠራ ዝንባሌ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ መንግስት የወጣቶችን ተሳተፎ ለማሳደግና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የስታርት አፕ አዋጅ በማጽደቅ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል፡፡ የፈጠራ ሀሳቦች ስታርት አፕ መሆናቸው በህግ ተለይቶ ምዝገባና ስያሜ ከተሰጠ በኋላ አስፈላጊው የፋይናንስና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ አዋጁን ገቢራዊ ለማድረግ ሀገር አቀፍ የስታርት አፕ ፖርታል እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው፤ የማስፈጸሚያ ደንቦችና መመሪያዎች ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሸገር ከተማ ለተገልጋዮች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Oct 18, 2025 162
ሸገር፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተገልጋዮች ተናገሩ። በሸገር ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ከተመዘገቡት ከ11ሺህ 224 ተገልጋዮች አብዛኞቹ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን እንደገለጹም ተመላክቷል። ከተጠቃሚዎቹ መካከል በአስተዳደሩ የፉሪ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሁዳ አብዱልከሪም፤ በአሁኑ ወቅት በማዕከሉ እያገኙት ያለው አገልግሎት በእጅጉ መሻሻሉን ለኢዜአ ተናግረዋል። ከዚህ በፊት አገልግሎት ለማግኘት ውጣ ውረድ ብሎም ላልተገባ ወጪ ሲዳረጉ እንደነበር አውስተው፤ አሁን ላይ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚፈልጉትን አገልግሎት በማግኘት ምቹ ሁኔታ አንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል። ቀደም ሲል በነበረው አገልግሎት ፋይል የመጥፋት አጋጣሚና ሌሎችም ችግሮች እንደነበር በማስታወስ አስተያየት የሰጡት ደግሞ ከገላን ክፍለ ከተማ የመጡ አቶ ወርቅነህ በንቲ ናቸው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ አገልግሎት ሰጪ ባለሙያዎቹ መልካም ስነምግባር በመላበስ ከአስር ደቂቃ በታች ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት እንደሚያስተናግዱና በዚህም መደሰታቸውን ተናግረዋል። ሌላው ተገልጋይ ከኩራጅዳ ክፍለ ከተማ የመጡት አቶ ሀብታሙ ጆቴ፤ በከተማው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ከ15 ደቂቃ ባነሰ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኙ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኦፕሬሽን ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ካሳሁን ጆብር እንዳሉት፤ ቀደም ሲል በከተማው የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በተበታተነና በተራራቀ መልኩ የሚያካሄዱት አሰራር በቴክኖሎጂ ያልተደገፈና የመረጃ ስርዓቱ ያልተሟላ ነበረ ። አገልግሎቱን ለማሻሻል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በማስጀመር የሚያስፈልጉትን ቴክኖሎጂና የሰው ሃይል በማሟላት ለማሕበረሰቡ ተደራሽ፤ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል። ይህ አሰራር ከተጀመረ በሶስት ወራት ውስጥም ከተመዘገቡት ከ11ሺ224 ሰዎች ውስጥ አስር ሺህ ሰዎች አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣይ አገልግሎቱን የበለጠ በማስፋፋት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ለባለሙያው የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ተገልጋዮች የሚጠበቅባቸውን አሟልተው እንዲገኙ ግንዛቤ ከመስጠት ጎን ለጎን በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መመቻቸቱን አስረድተዋል። በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ከሸገር ከተማ በተጨማሪ በቢሾፍቱ፤ አዳማ፤ ሻሸመኔና ጅማ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩ የሚታወስ ነው።
የልህቀት ማዕከሉ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የሚቆም ሚዲያ እና ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተላበሰ ጋዜጠኛ ለመፍጠር ያስችላል
Oct 18, 2025 201
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡- የሚዲያ ልህቀት ማዕከል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የሚቆም ሚዲያ እና ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተላበሰ ጋዜጠኛ ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ለሀገር ግንባታ፣ ለዜጎች የመረጃ ተደራሽነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና እንዲኖረው የዓለምን ነባረዊ ሁኔታ የዋጀ የዘርፉ ባለሙያ እና ቴክኖሎጂ መታጠቅ አለባቸው፡፡ በኢትዮጵያ ከለውጡ በኋላ የመገናኛ ብዙኃንና ጋዜጠኞች ዘርፉ የሚጠይቀውን ሙያዊ ሥነ ምግባር ተላብሰው ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ተደራሽነት በነፃነት መስራት የሚችሉባቸው የህግና የአሰራር ማሻሻያዎች ተደርገዋል፡፡ በቅርቡም የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን ዕውቀትና ክህሎት በምርምር፣ በማማከርና ስልጠና ማሳደግ የሚያስችል የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ሥራ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ አዲስ አበባን ጨምሮ በ25 ዩኒቨርሲቲዎች የጋዜጠኝነት ትምህርት እየተሰጠ ነው፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርቱን መስጠታቸው ትልቅ ነገር መሆኑን ያወሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ሆኖም አብዛኞቹ የጋዜጠኝነት ምሩቃን የንድፈ ሃሳብ እንጂ የተግባር ዕውቀትና ክህሎት እንደሚጎድላቸው ለይተናል ብለዋል፡፡ ጋዜጠኝነት ጽንሰ ሀሳቡን ተረድቶ ትንታኔ መስጠትና ማብራራት ቢሆንም ክፍተት ይታያል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በሥራ ላይ ያሉ ጋዜጠኞች ተለዋዋጭ ከሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር በየጊዜው መዘመን እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ውስን ዓላማን ብቻ ለማስፈፀም እንደነበር ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ምን ዓይነት ጋዜጠኝነት ትፈልጋለች የሚለውን መመለስ የሚያስችል የተቀናጀ ስልጠና አልነበረም ብለዋል፡፡ ጋዜጠኝነት ከዓለም ነባራዊ አውድ ጋር የተጣጣመ ቀጣይነት ያለው ዝማኔ ይፈልጋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የኢትዮጵያ የሚዲያ ልህቀት ማዕከልን ማቋቋም ማስፈለጉን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ኢትዮጵያን የሚመስል ዘመኑን የዋጀ የመገናኛ ብዙኃንና የጋዜጠኝነት ሙያ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ግቡ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ለሀገር ግንባታ የሚቆም፣ ለዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚተጋ የመገናኛ ብዙኃንና ጋዜጠኛ ማፍራት መሆኑን አንሰተዋል፡፡ በዚህም የልህቀት ማዕከሉ በብቁ የሰው ሀይል እና በቴክኖሎጂ የተሟላ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ጋዜጠኛውን ብቻ ሳይሆን መገናኛ ብዙኃንን ጭምር እንዲያልቅ እንፈልጋለን ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በጥናትና ምርምር፣ ስልጠናና በማማከር ሀገር በቀል እሳቤዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በዓለም ላይ ጋዜጠኝነት ከጥቅል ወደ ልዩ ዘጋቢነት እየተቀየረ መሆኑን በማስታወስ፤ ጋዜጠኞችን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በምርጫ፣ ውሃ፣ ፋይናንስ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ አቬሽን ጋዜጠኝነትና መሰል ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በማሰልጠንና በማብቃት የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ማዕከሉ የምርጫ ጋዜጠኝነት ስልጠና በቅርቡ እንዲሚጀምር በመጥቀስ፤ ከስድስት ዩኒቨርሲቲዎች በመጡ 32 ፕሮፌሰሮች 11 የሥልጠና ሰነዶች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ለሶስት ወራት በሚሰጠው የምርጫ ጋዜጠኝነት ሥልጠና የተዘጋጁ ሰነዶች የኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ፣ ሚዲያና ዲሞክራሲ፣ ሚዲያና ብሔራዊ ጥቅም፣ ምርጫና የዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ልምድ፣ እንዲሁም ሚዲያ ማህበረሰብና ባህል የሚሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ስፖርት
በሻምፒዮንስ ሊጉ የአርሰናል እና አትሌቲኮ ማድሪድ ጨዋታ ይጠበቃል
Oct 21, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ):- በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሶስተኛ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ። አርሰናል እና አትሌቲኮ ማድሪድ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኤምሬትስ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የተመልካቾች ትኩረት አርፎበታል። ሁለቱ ክለቦች በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ቡድኖቹ ከዚህ ቀደም በአውሮፓ መድረክ የተገናኙት እ.አ.አ በ2017/18 በዩሮፓ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ ነበር። በወቅቱ በኤምሬትስ በተካሄደው ጨዋታ አንድ አንድ አቻ ተለያይተው በመልሱ ጨዋታ አትሌቲኮ በሜዳው 1 ለ 0 በማሸነፍ በድምር ውጤት ለፍጻሜ አልፏል። የማድሪዱ ክለብ በፍጻሜው ማርሴይን በማሸነፍ ዋንጫውን ማንሳቱ አይዘነጋም። በሊግ ምዕራፍ የደረጃ ሰንጠረዥ አርሰናል በስድስት ነጥብ፤ አትሌቲኮ ማድሪድ በሶስት ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። አርሰናል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በ19 ነጥብ እየመራ ሲሆን አትሌቲኮ ማድሪድ አትሌቲኮ ማድሪድ በ16 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ጠንካራ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። የ44 ዓመቱ ጣልያናዊ ዳቪዴ ማሳ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌሎች መርሃ ግብሮች በቤይ አሬና ባየር ሌቨርኩሰን የወቅቱን የውድድሩ አሸናፊ ፒኤስጂን ምሽት 4 ሰዓት ላይ ያስተናግዳል። ቪያሪያል ከማንችስተር ሲቲ፣ ኮፐንሃገን ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ፣ ኒውካስትል ዩናይትድ ከቤኔፊካ፣ ፒኤስቪ አይንድሆቨን ከናፖሊ እና ዩኒየን ሴይንት ጊሎይስ ከኢንተር ሚላን በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ባርሴሎና ከኦሎምፒያኮስ እና ካይራት አልማቲ ከፓፎስ በተመሳሳይ ምሽት 1 ሰዓት ከ45 ላይ የሚካሄዱ ጨዋታዎች ናቸው።
ባህር ዳር ከተማ እና ምድረ ገነት ሽሬ ድል ቀንቷቸዋል
Oct 20, 2025 112
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10 /2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሃ ግብር ባህር ዳር ከተማ እና ምድረ ገነት ሽሬ ተጋጣሚዎቻቸውን በማሸንፍ ዓመቱን በድል ጀምረዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 3 ለ 1 አሸንፏል። ክንዱ ባየልኝ፣ አማኑኤል ገብረሚካኤል እና ሳቲ ኦሴ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጫላ ተሺታ ለሀድያ ሆሳዕና ብቸኛዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። የሀድያ ሆሳዕናው ኤልያስ መሐመድ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው ጨዋታ ምድረ ገነት ሽሬ በዳንኤል ዳርጌ ግብ መቀሌ 70 እንደርታን 1 ለ 0 አሸንፏል። አስቀድሞ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን ከአዳማ ከተማ ጋር ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ውጤቶቹን ተከትሎ የአንደኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳሉ።
ኢትዮጵያ መድን እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
Oct 20, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10 /2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ መድን እና አዳማ ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ዛሬ ከቀትር በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የአዳማ ከተማው ሃይደር ሸረፋ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። ሃይደር አምና በአምበልነት ኢትዮጵያ መድንን እየመራ የሊጉን ዋንጫ ማንሳቱ የሚታወስ ሲሆን ኮከብ ተጫዋች ሆኖ ተመርጦም ነበር። ኢትዮጵያ መድን የዋንጫ ክብሩን የማስጠበቅ ጉዞውን ነጥብ በመጣል ጀምሯል። በሌሎች የአንደኛ ሳምንት መርሃ ግብሮች ባህር ዳር ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና በአዲስ አበባ ስታዲየም፣ ምድረ ገነት ሽሬ ከመቀሌ 70 እንደርታ ጋር በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተመሳሳይ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ኢትዮጵያ መድን የዋንጫ ክብሩን የማስጠበቅ ጉዞውን ከአዳማ ከተማ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ይጀምራል
Oct 20, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10 /2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከነዚህ መርሃ ግብሮች መካከል አዳማ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ የሚያደርጉት ጨዋታ ይገኝበታል። ኢትዮጵያ መድን በ2017 ዓ.ም የውድድር ዓመት በ73 ነጥብ የሊጉን ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ማንሳቱ ይታወቃል። ተጋጣሚው አዳማ ከተማ አምና በሊጉ በ39 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። መድን የዋንጫ ክብሩን አስጠብቆ ለመቆየት የሚያደርገውን ጉዞ ዛሬ ይጀምራል። በአንጻሩ አዳማ ከተማ ባለፈው የውድድር ዓመት ከነበረው ደካማ አቋም የተሻለ እንቅስቃሴ ለማድረግ ይጫወታል። ቡድኖቹ በ2017 ዓ.ም በሊጉ ሁለት ጊዜ ተገናኝተው ኢትዮጵያ መድን ሁለቱንም ጨዋታዎች ማሸነፉ የሚታወስ ነው። በሌላኛው መርሃ ግብር ባህር ዳር ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ምድረገነት ሽሬ ከመቀሌ 70 እንደርታ ከቀኑ 10 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታል።
አካባቢ ጥበቃ
በአማራ ክልል ከ260 ሺህ ሄክታር በሚልቅ መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ እቀባ ሥራ ይከናወናል
Oct 18, 2025 208
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዚህ ዓመት ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራዎች እንደሚከናወኑ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ንቅናቄ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ ልቼ ቀበሌ ተካሂዷል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) የተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ስራ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ካልመጣ የመስኖ ስራ ውጤታማ እንደማይሆን ገልጸዋል። ክልሉ በመስኖ መልማት የሚችል ሰፊ አቅም እንዳለው ተናግረዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግ በዚህ ዓመት ከ52 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዲስ መስኖ በማስገባት የክልሉን የመስኖ ልማት ወደ 383 ሺህ ሄክታር ከፍ ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቁመዋል። ከተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ስራዎች አንጻርም በዚህ ዓመት ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። ይህንንም ለማድረግ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን የሚሆን የደን እና የፍራፍሬ ችግኝ ልማት እቅድ ተይዞ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል። የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ዝግጅቶቹ የመስኖ አውታር ግንባታ፣ የቅየሳ፣ የአርሶ አደሮች ስልጠና እንዲሁም የችግኝ ጣቢያዎች ግንባታ እና የእርሻ መሳሪያ ዝግጅቶችን ያካተተ መሆኑን አንስተዋል። በተደረጉ ጥናቶች ክልሉ በመስኖ ሊለማ የሚችል 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት እንዳለው ገልጸዋል። ይህንን ለማልማትም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ ረገድ ባለፉት ዓመታት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በርካታ የውሃ መሳቢያ መሳሪያዎች ወደ ዞኖች እና ወረዳዎች መከፋፈሉን ገልጸው ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል ስራ መሆኑን ገልጸዋል።
ምርታማነትን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር ይገባል
Oct 18, 2025 145
አዳማ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፡-ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ የንቅናቄ ሳምንት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ዛሬ ተጀምሯል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ በወቅቱ እንዳመለከቱት፥ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራዎች የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር፣ድርቅና የጎርፍ አደጋዎችን ለመመከት አግዘዋል። በተለይም በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኖችን የመንከባከቡ ስራ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ለመቋቋምና የተራቆቱ መሬቶች እንዲያገግሙ፣የደረቁ ሃይቆች፣ወንዞችና ዥረቶች ተመልሰው ለመስኖና ለተለያዩ ልማቶች እንዲውሉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። በበጋ ወቅት የተገነቡ የተፋሰስ ልማቶችን በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ በመሸፈንና በመንከባከብ ውጤት መገኘቱንም አንስተዋል። ተግባሩንም ለማዝለቅ የችግኝ እንክብካቤ የንቅናቄ ሳምንትን በማወጅ በዛሬው ዕለት የክልሉ ግብርና ሴክተር አመራሮችና ሰራተኞች በምስራቅ ሸዋ ዞን ማስጀመራቸውን ጠቁመዋል። በችግኝ እንክብካቤው አረም በማንሳት፣የመኮትኮትና ውሃን በማጠጣት ችግኞቹ የበጋውን ወቅት እንዲቋቋሙ መስራት ይገባል ብለዋል። በንቅናቄው ማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት ከድር መሐመድ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ እንዲያድጉ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ችግኝ መትከል ብቻውን ግብ እንዳልሆነ ተናግረው፤የተተከሉትን ችግኞች በየጊዜው በመንከባከብ ለውጤት እንዲበቁ ማድረግ አለብን ብለዋል። ዘርፌ ማሞ በበኩሏ፥ በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ በቀዳሚነት የሚጎዱት ሴቶች በመሆናቸው ለመፍትሔው ላለፉት ሰባት ዓመታት በችግኝ ተከላና እንክብካቤ ላይ መሳተፋቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ ናት- ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)
Oct 16, 2025 231
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርኃ ግብር አካሂዷል። በመርኃ ግብሩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያሥላሴ፣ ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተገኝተዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ምላሽ ለመስጠት ያለንን ቁርጠኝነት ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። ጉባዔው አፍሪካውያን ለአየር ንብረት ለውጥ ተጨባጭ መፍትሔዎችን በመውሰድ ግንባር ቀደም መሆናቸውን ለዓለም በማሳየት ስኬታማ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም ለጋራ ችግሮች በጋራ ምላሽ ለመስጠት አቅማቸውን ያጠናከሩበት እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ይህን ስኬት ተጠቅሞ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት የሥራ ዕድል ፈጠራ ውጤታማ ተግባር እያከናወነች ትገኛለች
Oct 16, 2025 198
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል በአፍሪካ ግንባር ቀደም የሆነ ተግባር እያከናወነች መሆኑ ተገለጸ። ይህ የተገለጸው "አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችና ወጣቶች" በሚል ርዕስ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የተጠና ጥናት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ይፋ በሆነበት መድረክ ላይ ነው። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት እና የጥናቱ መሪ ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና እንደገለጹት የአረንጓዴ ልማት ስራ ዕድል ፈጠራ የአካባቢን ዘላቂነት ከማረጋገጥ ባሻገር ለወጣቶች ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል ወሳኝ ሚና አለው። ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የአካባቢ ጥበቃን በማጠናከር ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር በአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ተግባር እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይ በአረንጓዴ ልማት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል በሁሉም ሴክተሮች በማስፋት የወጣቱን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማትን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል። በመሆኑም በተለይ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የአረንጓዴ የስራ ዕድል የሚፈጥሩ ስልጠናዎች ተገቢ ትኩረት እንዲያገኙ እንዲሁም በፖሊሲዎች ውስጥ ልዩ ትኩረት እንዲሰጣቸው በማድረግ ሊበረታቱ እንደሚገባም አመልክተዋል። የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለበል ደሴ በበኩላቸው፣ ጥናቱ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ዕድገት ስትራቴጂዎችና የወጣቶች የሥራ ስምሪት ዕቅዶችን እንደሚደግፍ ጠቅሰዋል። ግኝቶቹ ወደ ተግባራዊ ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞች እንዲተረጎሙ ከሚመለከታቸው የመንግስት መሥሪያ ቤቶች እና የልማት አጋሮች ጋር በቀጣይ እንደሚሰራበት ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የአካባቢ ጥበቃን የሚያጠናክር አረንጓዴ ሥራዎች ሙያዊ ሥልጠና ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የአካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ገነነ አበበ(ዶ/ር) ናቸው። በቀጣይ የአረንጓዴ ሥራን ይበልጥ ለማስፋፋት በተለይ በቀጣሪ መሥሪያ ቤቶችና ሌሎች ተቋማት ላይ የግንዛቤ ሥራ ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በቀጣናው መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከል የተጀመሩ የቅንጅት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኢጋድ
Oct 20, 2025 106
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኢጋድ ሶስተኛው የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ በኬንያ ናይሮቢ ተጀምሯል። “በኢጋድ ቀጣና ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሰራተኛ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር ህጋዊ ማዕቀፍን ማሻሻል” የስብሰባው መሪ ቃል ነው። በስብሰባው ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት የሰራተኛ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች፣ ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(አይኤልኦ)፣ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(አይኦኤም)፣ የአውሮፓ ህብረትና የልማት አጋሮች ተገኝተዋል። በኢጋድ ቀጣና የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በቀይ ባህር መስመር ያለውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ከኢጋድ ቀጣና ውጪ የሚገኙ ዜጎች አባል ሀገራትን በነጠላ የመግቢያ ቪዛ መጎብኘት የሚያስችላቸውን የቪዛ ኢኒሼቲቭ ይፋ ይደረጋል። ኢኒሼቲቩ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርና ድንበር ተሻጋሪ ንግድን ማሳለጥ እንዲሁም ቱሪዝምን የማሳደግ ፋይዳ እንዳለው ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአውሮፓ ህብረት የፋይናንስ ድጋፍ የሚተገበረው ነጻ የሰዎችና የቁም እንስሳት እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፍ ሁለተኛ ምዕራፍ ይፋ ይሆናል። ማዕቀፉ ህጋዊ የፍልሰት መንገዶች ለማጠናከር እና ቀጣናዊ ትስስርን የማሳካት ግብ ያለው መሆኑንም አመልክቷል። ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሰንሰለትን መበጣጠስ፣ በፍልሰት በሌላ ሀገር የሚገኙ ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ላይ ምክክር ያደርጋሉ። በውይይቱ ማብቂያ ሀገራት የጋራ መግለጫ እንደሚያወጡ የሚጠበቅ ሲሆን ደህንነቱ የተጠበቀ መደበኛ ፍልሰት፣ ጠንካራ የሰራተኛ አስተዳደር ስርዓት መፍጠርና ለሰዎች ዝውውር የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ መስጠት ላይ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እንደሚገልጹ ተጠቁሟል። ኢጋድ በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የጋራ ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክቷል። ዜጎች ህጋዊ አማራጮችን እንዲከተሉና የኢኮኖሚ ፈተናን ጨምሮ ለሌሎች ገፊ ምክንያቶች ዘላቂ መፍትሄ መስጠት በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ ገልጿል። ስብሰባው ጥቅምት 10 እና 11 በባለሙያዎች፣ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚኒስትሮች ደረጃ ይካሄዳል።
የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በቁርጠኝነት ሊተገብሩ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት
Oct 19, 2025 175
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) አፈጻጸም ውጤታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብስባ ከጥቅምት 11 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገም እና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስ እና ዘላቂ የውሃና ተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚከናውን ኢዜአ ከህብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ
Oct 15, 2025 329
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር እና በአህጉሪቷ የማካካሻ ፍትህን ለማረጋገጥ በበለጠ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን በአፍሪካ ደረጃ ዛሬ በአህጉሪቷ መዲና አዲስ አበባ ዛሬ ይከበራል። “የገጠር ሴቶችን በማካካሻ ፍትህ አማካኝነት ማብቃት፤ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ስርዓተ ምግብን ማረጋገጥ” የቀኑ መሪ ሀሳብ ነው። በቀኑ አከባበር ላይ የአፍሪካ ህብረት አመራሮች፣ የመንግስታት ተወካዮች፣ የገጠር ሴቶች አመራሮች እና ተወካዮች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ የዳያስፖራ ተወካዮች፣ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ይሳተፋሉ። የቀኑ አከባበር አካል የሆነ የቴክኒክ ውይይት ትናንት የተካሄደ ሲሆን የአፍሪካ የገጠር ሴቶች መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ባለሙያዎች ሴቶችን ለማብቃት በየሀገራቱ እየተተገበሩ ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ የእውቀት እና የተሞክሮ ልውውጥ አድርገዋል። ዛሬ በሚኖረው ዋናው የቀኑ አከባበር የከፍተኛ ባለስልጣናት ቁልፍ ንግግሮች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የገጠር ሴቶች ኢኒሼቲቭ የተሞክሮ ማጋራት መርሃ ግብሮች እና አውደ ርዕዮች ይካሄዳሉ። ሁነቶቹ የገጠር ሴቶች በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እና በግብርና መካናይዜሽን አማካኝነት የሚበቁባቸው የኢኖቬሽን አማራጮች የሚቀርቡባቸው ናቸው። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን ከአፍሪካ ህብረት የ2025 መሪ ሀሳብ ከሆነው “የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” የተሳሳረ መሆኑ ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የማሻሻሻ ፍትህ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አካሄድ መሆኑን አመልክቷል። የቀኑን አከባበር ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የጋራ መግለጫው አፍሪካ ስርዓተ ጾታን ባማከለ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ስራ፣ የገጠር ሴቶችን በማብቃት እንዲሁም ማካካሻ ፍትህ እኩልነት የተረጋገጠበትና የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመገንባት ያላትን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት እንደሆነ ተገልጿል። የዓለም የገጠር ሴቶች ቀን የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማረጋገጥ እና በማካካኛ ፍትህ አማካኝነት በገጠሪቷ የአፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። ህብረቱ ቀኑን ሲያከብር የበለጸገች፣ ሁሉን አቃፊ እና ዘላቂነትን ያረጋገጠች አህጉር ለመገንባት ባለው መሻት ውስጥ ሴቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ወደኋላ እንዳይቀሩ ዳግም ቃል ኪዳኑን የሚያድስበት እንደሆነ አመልክቷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እ.አ.አ በ2007 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ባፀደቀው የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 62/136 አማካኝነት ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን እ.አ.አ ኦክቶበር 15 እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ በገጠር የሚገኙ ሴቶች ለግብርና፣ ምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ዘላቂ ልማት ያላቸው ወሳኝ አበርክቶዎች የሚዘከርበት ነው።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በሙሉ አቅም መተግበር ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው - መሐመድ አሊ ዩሱፍ
Oct 10, 2025 461
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ሙሉ ለሙሉ ገቢራዊ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁነቶች በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት እና ተወዳዳሪነት ተጽእኖ እያሳደሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከመቼው ጊዜ በላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ ለሙሉ በአፋጣኝ መተግበር እንደሚገባው የሚያመላክት ነው ብለዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ከቀረጥ ጋር ያልተያያዙ የንግድ ገደቦችን በማንሳት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተሳለጠ የንግድ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችሉ ማዕቀፎችን በመተግበር ለአጀንዳ 2063 መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኮሜሳ፣ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳዴቅ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) የሶስትዮሽ ትብብር ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕቀፉ የትስስር አጀንዳ ተምሳሌት እና አንድ የሆነች፣ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች አህጉር ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ቀጣናዊና አህጉራዊ የትስስር አጀንዳዎችን ትግበራ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 355
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 471
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 673
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
"ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 759
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ። አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው። ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል። ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡ ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1108
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1792
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2605
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2751
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 422
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 372
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6221
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4699
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የአፍሪካ የግብርና፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ፤ እድሎች እና ፈተናዎች
Oct 20, 2025 154
አፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማሳካትና እንድትበለጽግ የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ መዕራፍ ላይ ይገኛል። የአህጉሪቱን የመለወጥ ትልም ባሏት እምቅ ተፈጥሯዊ ጸጋዎች ላይ የተመረኮዘ ነው። ተዝቆ የማያልቀው የአፍሪካ ብዝሃ ሀብት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግና አይበገሬ አቅም መገባንት የሚያስችሏትም ጭምር ናቸው። ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ ሀብቶቿ እና ብዝሃ ከባቢ የአየር ንብረቷ ከሀብቶቿ መካከል ይጠቀሳሉ። ግብርና አሁንም የአፍሪካ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው። ዘርፉ ለአህጉሪቱ 35 በመቶ የሚጠጋ አጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት(ጂዲፒ) አስተዋጽኦ ያደርጋል። 60 በመቶ ህዝብም በግብርና ስራ እንደሚተዳደር የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) ሰነድ ያሳያል። ከዚህም ውስጥ አብዛኞቹ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። ሴቶች በግብርናው ዘርፍ ካለው የሰው ኃይል የ50 በመቶ ድርሻው ይወስዳሉ። የአፍሪካ ህዝብ 60 በመቶ ድርሻ የያዘው ወጣት በግብርና ንግድ፣ እሴት መጨመርና የኢኖቬሽን ስራዎች ያለው ተሳትፎ እያደገ መጥቷል። የዓለም 60 በመቶ ያልለማ መሬት ያለው በአፍሪካ ነው። ሰፊ የውሃ ሀብቶችና እያደገ ያመጣው ብሉ ኢኮኖሚ(የባህር እና ሌሎች የውሃ ሀብቶች) ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ እድገትን የሚያረጋግጡ ናቸው። የመሰረተ ልማቶች ተደራሽነት ማደግ፣ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችና ኢኖቬሽንን የተመረኮዙ የፋይናንስ አማራጮችን መስፋት ግብርናን የምግብ ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለኢንዱስትሪ ልማት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ እና ንግድ መሳለጥ ትልቅ አቅም መሆን ይችላል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በግብርና ምርቶችና አገልግሎቶች ያለውን አህጉራዊ የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ በማሳደግ ረገድ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ ነው። የንግድ ቀጣናውን በሚገባ መጠቀም ከተቻለ እ.አ.አ በ2030 የግብርና ንግድ ልውውጡን በ30 በመቶ ማሳደግ እንደሚቻል ጥናቶች ያመለክታሉ። ግብርናው የተጠቀሱት ጥንካሬዎች ያሉት ቢሆንም ረጅም ጊዜ የዘለቁ መዋቅራዊ ፈተናዎች አብረውት ዘልቀዋል። የግብርና ምርቶች ላይ የሚፈለገውን ያህል እሴት አለመጨመር፣ የቴክኖሎጂ አጠቀቃምና የምርታማነት ውስንነት፣ የመሰረተ ልማቶች እና ሎጅስቲክስ በበቂ ሁኔታ አለመሟላት፣ ተቋማዊና አስተዳደራዊ ክፍተቶች ከአየር ንብረት ለውጥና ሌሎች ተፈጥሯዊ አደጋዎች እንዲሁም እያደገ ከመጣው ህዝብ ጋር ተዳምሮ ግብርናውን እየፈተነው ይገኛል። ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ማጠንጠኛ የሆነው ጉዳይ የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት(ካዳፕ) ነው። እ.አ.አ በ2003 የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ ባደረገው ስብሰባ የግብርና የምግብ ዋስትና ድንጋጌን አጽድቋል። ይህ ማዕቀፍ የማፑቶ ድንጋጌ ስያሜን በማግኘት የካዳፕ ትግበራ በይፋ እንዲጀመር አድርጓል። የማፑቶ ድንጋጌ እ.አ.አ በ2014 በማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025 የተተገበረ) በአዲስ መልክ የታደሰ ሲሆን የተለያዩ ቃል ኪዳኖችን በውስጡ ይዟል። ይህም በካዳፕ አማካኝነት የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ከአጠቃላይ ዓመታዊ ጥቅል ምርታቸው(ጂዲፒ) ቢያንስ ስድስት በመቶውን ለግብርናው ዘርፍ እንደሚመድቡና በየሀገራቱ በዘርፉ በየዓመቱ በአማካይ ስድስት በመቶ እድገትን የማሳካት ግብ አለው። ረሃብን ማጥፋት፣ ድህነትን በግማሽ መቀነስ፣ የማይበገር አቅም መገንባትና የጋራ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ሌሎች ግቦች ናቸው። ካዳፕ የአፍሪካ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ያላቸውን ኢንቨስተመንት በማሳደግ፣ በአፍሪካ የእርስ በእርስ የግብርና ንግድን በማሳደግና የፖሊሲ መሰናሰልን በመፍጠር ቁልፍ ሚና ተወጥቷል። ይሁንና የተመዘገቡት ውጤቶች ያልተመጣጠነ ልዩነት የሚታይባቸው ናቸው። የ2023 የካዳፕ የግምገማ ሪፖርት እንደሚያሳየው የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የማላቦ ግቦችን ማሳደግ የሚያስችል መንገድ ላይ እንዳልሆኑ ያስቀምጣል። ይሁንና 26 ሀገራት በተቀመጡ ግቦች መመዘኛ መሻሻል እንዳሳዩ ይገልጻል። ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ካሜሮን፣ ግብጽ፣ ማሊ፣ ጋና እና ጋምቢያ የተሻለ አፈጻጸም ካላቸው ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ። አብዛኞቹ ሀገራት በግብርና ኢንቨስትመንት፣ ምርታማነት እና የፖሊሲ ትግበራ ላይ ፈተናዎች እንዳሉበት ሪፖርቱ አመልክቷል። ሀገራት የሰነዱን ትግበራ ማፋጠንና ተቋማዊ ቅንጅትን ማጠናከር እንደሚገባቸው አሳስቧል። የማላቦ ድንጋጌ ወደ መገባደዱ ላይ የሚገኝ ሲሆን የካዳፕ ቀጣዩ ምዕራፍ የካምፓላ ድንጋጌ ነው። ይህ የትግበራ ምዕራፍ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚቆይ ነው። የካምፓላ ድንጋጌ ከማፑቶ እና ማላቦ ድንጋጌዎች ትምህርቶችን በመውሰድ የግብናውን እድገት ማላቅ ግቡ አድርጎ ይዟል። የካምፓላ አጀንዳ ኢኖቬሽን፣ ዲጂታላይዜሽን፣ አረንጓዴ እድገት እና አይበገሬነት ያላቸውን ሚና በማንሳት መስኮቹ ስርዓተ ምግብን ዘላቂና አካታች የማድረግ ግብን ማሳካት እንደሚያስችሉ አመልክቷል። በዚህ ማዕቀፍ እ.አ.አ 2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ህዝብ ይኖራታል ተብሎ የሚጠበቀውን አፍሪካን በራስ አቅም የመመገብ ውጥን የያዘ ነው። ይሁንና የግብርና ምርታማነት ከዓለም አቀፍ አማካይ የምርታማነት ምጣኔ አንጻር ሲታይ አሁንም ወደ ኋላ ቀረት ያለ ነው። ይህም አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች የተገደበ የፋይናንስ አቅርቦት ማግኘታቸው እንዲሁም የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትና የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው አለመደረጉ የችግሩ አብይ መንስኤ ሆኖ ይጠቀሳል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎችና የከባቢ አየር ብክለት ፈተናዎቹ እንዲበረቱ አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ የበይነ መንግስታት ፓናል(IPCC) አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እርምጃዎችን በፍጥነት ካልወሰደች እ.አ.አ በ2050 የግብርና ምርታማነቷ ከ20 እስከ 30 በመቶ ሊቀንስ እንደሚችል ገምቷል። ከ250 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ አፍሪካውያን ደህንነቱ ያልተረጋገጠ እና ንጽህናው ያልተጠበቀ የውሃ አቅርቦት ፈተና ውስጥ ይገኛሉ። በህዝብ ቁጥር መጨመር፣ በከተሜነትና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ምክንያት ንጹህ የውሃ አቅርቦትን የማግኘት ጉዳይ የበለጠ ሊስፋ እንደሚችል ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩና ፈተናዎች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ለአባል ሀገራት የፋይናንስ እና የቴክኒክ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል። የህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር የስራ ክፍሉ(DARBE) አማካኝነት የአፍሪካን ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞችና ኢኒሼቲቮች የተናበቡና የጋራ ግብ ያላቸው እንዲሆኑ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል። የአቅም ግንባታ፣ የቴክኒክ እና የፖሊሲ ድጋፍም የሚያደርግ ሲሆን ብሄራዊ እቅዶች ከአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሰነዶችና የአጋርነት ማዕቀፎች ጋር የተጣጠሙ መሆናቸውን ያረጋገጣል። የስራ ክፍሉ ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች ጋር አጋርነቶችን የማጠናከር ስራ ያከናውናል። ግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት እንዲሁም የተፈጥሮ እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በዘላቂነት መጠቀም ላይ የተቀናጁ አሰራሮችን መፍጠር ላይም ይሰራል። የዘርፉ አጠቃላይ ስራዎች አካል የሆነው ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎችና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገምና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም(ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ(ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስና ዘላቂ የውሃና የተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩም ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚያከናውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። አፍሪካ ወደ ዘላቂ ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር እና አካባቢ ጥበቃ እያደረገች ያለው ጉዞ አንገብጋቢ አጀንዳና ሽግግሩን ለማፋጠን ወሳኝ ሚና አለው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የፋይናንስ ማነቆ፣ መሰረተ ልማቶች እና የፖሊሲ የመፈጸም አቅም ውስንነትን ጨምሮ የተለያዩ ፈተናዎች ቢኖሩባትም እድሎቿ ፈርጀ ብዙ ናቸው። በርካታ ያልለማ መሬት፣ ሰፊ የውሃ ሀብት፣ ወጣቶች እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በአፍሪካ ዘላቂ የግብርና እድገት ለማረጋገጥና ሁሉን አቀፍ ስርዓተ ምግብ ለመገንባት የሚያስችል ነው። ለአርሶ አደሮች በቂ የፋይናንስ አቅርቦት ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ አቅማቸውን መገንባት ቁልፍ ጉዳይ ነው። ሀገራት ብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸውን ከአህጉራዊ ማዕቀፎች ጋር ማጣጣም ይኖርባቸዋል። ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ይገባል። የተፈጥሮ ሀብትን በሚገባ መጠቀም፣ በኢኖቬሽን ላይ መዋዕለ ንዋይን ፈሰስ ማድረግና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች፣ አረንጓዴ እና የበለጸገች አህጉር መገንባት ይቻላል።
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 869
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡ በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!