አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ በአፍሪካ የታዳጊ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የመክፈቻ ቀን አራት ሜዳልያዎችን አግኝታለች
Jul 17, 2025 41
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017 (ኢዜአ)፦ ሶስተኛው የአፍሪካ ከ20 እና 18 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ማምሻውን በናይጄሪያ አቡካታ ተጀምሯል። በመክፈቻው የኢትዮጵያ አትሌቶች የተሳተፉባቸው አምስት የፍጻሜ ውድድሮች ተካሄደዋል። በ1500 ሜትር ሴት ከ18 ዓመት በታች ፍጻሜ ኤልሳቤጥ አማረ የብር፣ ደስታ ታደሰ የነሐስ ሜዳልያ አግኝተዋል። አትሌት ትርሃስ ገብረህይወት በ3000 ሜትር ሴቶች ከ20 ዓመት በታች የፍጻሜ ውድድር የብር ሜዳልያ አግኝታለች። እንዲሁም በ1500 ሜትር ወንድ ከ18 ዓመት በታች ሳሙኤል ገብረሃዋርያ የነሃስ ሜዳልያ ለሀገሩ ማስገኘቱን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በስሉስ ዝላይ ሴት ከ20 ዓመት በታች ፍፃሜ ኛቾክ ቾል፣ አትሌት ንብረት ክንዴ በ10000 ሜትር ወንድ ከ20 ዓመት በታች ፍፃሜ ደረጃ ውስጥ አልገቡም። በአጠቃላይ በሻምፒዮናው መክፈቻ ኢትዮጵያ ሁለት ብር፣ ሁለት ነሐስ በድምሩ አራት ሜዳልያዎች አግኝታለች። ኢትዮጵያ በውድድሩ ላይ 30 ወንድ እና 27 ሴቶች በድምሩ 57 አትሌቶችን ታሳትፋለች። ሶስተኛው የአፍሪካ ከ20 እና 18 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
ልዩነትን ከግጭት በራቀ መልኩ በውይይት የመፍታት ባህል ሊዳብር ይገባል -የሀይማኖት አባቶች
Jul 16, 2025 81
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ልዩነትን ከግጭት በራቀ መልኩ በውይይት የመፍታት ባህል ሊዳብር እንደሚገባ የሀይማኖት አባቶች አሳሰቡ። በኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት አስተባባሪነት የሀይማኖት አባቶች በትግራይ መቀሌ ያደረጉትን የሰላም ጥሪ በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የሀይማኖት አባቶቹን በመወከል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እንደገለፁት፣ የሀይማኖት አባቶቹ በቆይታቸው ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ እና አመራራቸው እንዲሁም ከክልሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል።   የሀይማኖት አባቶቹ ለባለድርሻ አካላቱ የሰላም ጥሪ ማቅረባቸውንም ጠቁመዋል። የሀይማኖት አባቶቹ፣ በትግራይ ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መነጋገራቸውን ጠቅሰው፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፍታት እንደሚገባ ማስገንዘባቸውንም አስረድተዋል። ባለድርሻ አካላቱ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንደሚፈቱም ተስፋቸውን ገልፀዋል። የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤም በጉዳዩ ዙሪያ ያለውን በጎ አበርክቶ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ሀጂ ኢብራሂም አመልክተው፣ ልዩነትን ከግጭት በራቀ አኳሃን በውይይት ብቻ የመፍታት ባህል በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች ሊዳብር እንደሚገባም አሳስበዋል።
የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል
Jul 16, 2025 83
ድሬዳዋ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለፁ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬዳዋ ተካሂዷል። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ፤ በማጠቃለያ ንግግራቸው በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮችና መሰራት ስላለባቸው ቀጣይ አቅጣጫዎች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሀገርንና ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው በተለይም የኑሮ ውድነትን በማቃለል ረገድ በቀጣይ ብዙ ስራዎች ይጠበቃሉ ብለዋል። በዚህ ረገድ ጅምሮቹ ጥሩ መሆናቸውን አንስተው እንደየ ክልሎቹ ነባራዊ ሁኔታ ምርቶችን በመለየትና አቅርቦትና ምርታማነትን በማሳለጥ በቀጣይም ብዙ መስራት ይገባል ብለዋል። በምርት አቅርቦት ረገድ የክልሎች ትብብርና ጥብቅ ትስስር አስፈላጊ በመሆኑ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።   የቅዳሜ እና እሁድ ግብይቶችን ጨምሮ ለገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በየደረጃው ያሉ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት ተጨማሪ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው የኮንትሮባንድ ንግድንና የገበያ አሻጥሮችን በጥብቅ በመከታተል ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም በቅንጅት መስራት ይገባልም ብለዋል። የድሃ ተኮር ፕሮግራሞችን አጠናክሮ መቀጠል፣ የአመጋገብ ባህል እንዲሻሻል መጣርና የምርት አማራጮችን ማስፋትም እንዲሁ። ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር መልካም ጅምሮች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ አደም የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥልቀት በማየት በዘላቂነት መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም የብድር ሁኔታን የማመቻቸት፣ የስልጠና እድሎችን የማስፋትና የሰዎች የአስተሳሰብ በመለወጥ ረገድ እንዲሁም የስራ እና የመሸጫ ቦታዎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውሉ አመራሩ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከተረጅነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት ከቤተሰብ እቅድ ጀምሮ የድጋፍና ክትትል ስራን በማጠናከር ከሌማት ትሩፋትና ሌሎች የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ኢኒሸቲቮች ትግበራ ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዲፈጠር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል አቶ አደም። የሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠትና ዘላቂ መፍትሄ ለመሻትም የመጠባበቂያ ክምችትን ማሳደግና ጠንካራ የአሰራር ስርአት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል። ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በጥንቃቄ በመለየት ለፈጣን ምላሽ፣ በቂና የተሟላ ዝግጅት አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
መገናኛ ብዙሃን ሀገርን የሚገነቡ ተሻጋሪ ትርክቶች ላይ በትኩረት መስራት አለባቸው - አቶ ዛዲግ አብርሃ
Jul 16, 2025 103
  አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ሀገርን የሚገነቡ ዘመን ተሻጋሪ ትርክቶችን የመቅረጽ ሚናቸውን በተገቢው ሁኔታ መወጣት እንዳለባቸው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለጹ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት(ኢዜአ) አመራሮች እና ጋዜጠኞች ስልጠና እየሰጡ ይገኛል። አቶ ዛዲግ መገናኛ ብዙሃን መረጃን ከማቅረብ ባሻገር መሰረታዊ ለውጥን የሚያመጡ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባቸው ገልጸዋል። በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን ሀገርን ለመገንባትና ዜጎችንም ለጋራ ሀገራዊ ግብ በአንድነት እንዲቆሙ የሚያስችሉ የይዘት ስራዎች ላይ ማተኮር አለባቸው ብለዋል።   መገናኛ ብዙሃን ለሀገር ግንባታ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን ጠቅሰው የግንባታ ሂደቱን ከማሳለጥ አኳያ ገንቢ ሚና መጫወት እንዳለባቸው አንስተዋል። ጋዜጠኞችም ከዕለት ደራሽ ዜና ባለፈ አዎንታዊ ተጽእኖ የሚፈጥር ይዘት ሰርቻለሁ ወይ? በሚል ራሳቸውን በመፈተሽ ዘላቂነት ላላቸው ጉዳዮች ትኩረት መስጠትና ራሳቸውን ማብቃት እንደሚኖርባቸው አመልክተዋል። መገናኛ ብዙሃን ችግር ነቃሽ ብቻ ሳይሆኑ መፍትሄ አፍላቂ መሆን ይገባቸዋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለዚህም የጋዜጠኝነት ገንቢ ስራ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ዜጎች ላይ ተስፋን የሚጭሩ እና ብርሃን የሚያሳዩ መሆን እንዳለባቸውም ተናግረዋል። ድልድይ ሰዎችን እንደሚያገናኘው ሁሉ ትርክት የሰዎችን አዕምሮ ያገናኛል ያሉት ፕሬዝዳንቱ መገናኛ ብዙሃና የጋራ ትርክት ላይ በማተኮር ሀገር እና መንግስት ተቀራርበው እንዲሰሩ ምቹ መደላልድል መፍጠር እንደሚገባቸው አንስተዋል። ዘመን ተሻጋሪ የሚሆኑ ትርክቶችን በመቅረጽ፣ የህዝብ ድምጽ በመሆን እና ተቋማትን በማጠናከር ረገድ ጋዜጠኞች ወሳኝ ሚና አላቸው ብለዋል።   በተለይም ዜጎችን ትክክለኛ እና እውነተኛ መረጃ በማስታጠቅ እና ንቃተ ህሊናቸውን በማሳደግ ለሀገራቸው ጥቅም እና ፍላጎት እንዲቆሙ የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ነው ያሉት። ጋዜጠኛው ለፈተናዎች እና ለችግሮች እጅ ሳይሰጥ በአይበገሬነት በመስራት ሀገርን የሚገነቡ እና ትውልድን የሚቀርጹ ስራዎችን ማከናወን እንዳለባት አሳስበዋል።
የሚታይ
ልዩነትን ከግጭት በራቀ መልኩ በውይይት የመፍታት ባህል ሊዳብር ይገባል -የሀይማኖት አባቶች
Jul 16, 2025 81
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ልዩነትን ከግጭት በራቀ መልኩ በውይይት የመፍታት ባህል ሊዳብር እንደሚገባ የሀይማኖት አባቶች አሳሰቡ። በኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት አስተባባሪነት የሀይማኖት አባቶች በትግራይ መቀሌ ያደረጉትን የሰላም ጥሪ በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የሀይማኖት አባቶቹን በመወከል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እንደገለፁት፣ የሀይማኖት አባቶቹ በቆይታቸው ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ እና አመራራቸው እንዲሁም ከክልሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል።   የሀይማኖት አባቶቹ ለባለድርሻ አካላቱ የሰላም ጥሪ ማቅረባቸውንም ጠቁመዋል። የሀይማኖት አባቶቹ፣ በትግራይ ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መነጋገራቸውን ጠቅሰው፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፍታት እንደሚገባ ማስገንዘባቸውንም አስረድተዋል። ባለድርሻ አካላቱ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንደሚፈቱም ተስፋቸውን ገልፀዋል። የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤም በጉዳዩ ዙሪያ ያለውን በጎ አበርክቶ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ሀጂ ኢብራሂም አመልክተው፣ ልዩነትን ከግጭት በራቀ አኳሃን በውይይት ብቻ የመፍታት ባህል በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች ሊዳብር እንደሚገባም አሳስበዋል።
የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል
Jul 16, 2025 83
ድሬዳዋ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለፁ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬዳዋ ተካሂዷል። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ፤ በማጠቃለያ ንግግራቸው በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮችና መሰራት ስላለባቸው ቀጣይ አቅጣጫዎች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሀገርንና ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው በተለይም የኑሮ ውድነትን በማቃለል ረገድ በቀጣይ ብዙ ስራዎች ይጠበቃሉ ብለዋል። በዚህ ረገድ ጅምሮቹ ጥሩ መሆናቸውን አንስተው እንደየ ክልሎቹ ነባራዊ ሁኔታ ምርቶችን በመለየትና አቅርቦትና ምርታማነትን በማሳለጥ በቀጣይም ብዙ መስራት ይገባል ብለዋል። በምርት አቅርቦት ረገድ የክልሎች ትብብርና ጥብቅ ትስስር አስፈላጊ በመሆኑ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።   የቅዳሜ እና እሁድ ግብይቶችን ጨምሮ ለገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በየደረጃው ያሉ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት ተጨማሪ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው የኮንትሮባንድ ንግድንና የገበያ አሻጥሮችን በጥብቅ በመከታተል ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም በቅንጅት መስራት ይገባልም ብለዋል። የድሃ ተኮር ፕሮግራሞችን አጠናክሮ መቀጠል፣ የአመጋገብ ባህል እንዲሻሻል መጣርና የምርት አማራጮችን ማስፋትም እንዲሁ። ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር መልካም ጅምሮች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ አደም የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥልቀት በማየት በዘላቂነት መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም የብድር ሁኔታን የማመቻቸት፣ የስልጠና እድሎችን የማስፋትና የሰዎች የአስተሳሰብ በመለወጥ ረገድ እንዲሁም የስራ እና የመሸጫ ቦታዎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውሉ አመራሩ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከተረጅነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት ከቤተሰብ እቅድ ጀምሮ የድጋፍና ክትትል ስራን በማጠናከር ከሌማት ትሩፋትና ሌሎች የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ኢኒሸቲቮች ትግበራ ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዲፈጠር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል አቶ አደም። የሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠትና ዘላቂ መፍትሄ ለመሻትም የመጠባበቂያ ክምችትን ማሳደግና ጠንካራ የአሰራር ስርአት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል። ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በጥንቃቄ በመለየት ለፈጣን ምላሽ፣ በቂና የተሟላ ዝግጅት አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
መገናኛ ብዙሃን ሀገርን የሚገነቡ ተሻጋሪ ትርክቶች ላይ በትኩረት መስራት አለባቸው - አቶ ዛዲግ አብርሃ
Jul 16, 2025 103
  አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ሀገርን የሚገነቡ ዘመን ተሻጋሪ ትርክቶችን የመቅረጽ ሚናቸውን በተገቢው ሁኔታ መወጣት እንዳለባቸው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለጹ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት(ኢዜአ) አመራሮች እና ጋዜጠኞች ስልጠና እየሰጡ ይገኛል። አቶ ዛዲግ መገናኛ ብዙሃን መረጃን ከማቅረብ ባሻገር መሰረታዊ ለውጥን የሚያመጡ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባቸው ገልጸዋል። በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን ሀገርን ለመገንባትና ዜጎችንም ለጋራ ሀገራዊ ግብ በአንድነት እንዲቆሙ የሚያስችሉ የይዘት ስራዎች ላይ ማተኮር አለባቸው ብለዋል።   መገናኛ ብዙሃን ለሀገር ግንባታ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን ጠቅሰው የግንባታ ሂደቱን ከማሳለጥ አኳያ ገንቢ ሚና መጫወት እንዳለባቸው አንስተዋል። ጋዜጠኞችም ከዕለት ደራሽ ዜና ባለፈ አዎንታዊ ተጽእኖ የሚፈጥር ይዘት ሰርቻለሁ ወይ? በሚል ራሳቸውን በመፈተሽ ዘላቂነት ላላቸው ጉዳዮች ትኩረት መስጠትና ራሳቸውን ማብቃት እንደሚኖርባቸው አመልክተዋል። መገናኛ ብዙሃን ችግር ነቃሽ ብቻ ሳይሆኑ መፍትሄ አፍላቂ መሆን ይገባቸዋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለዚህም የጋዜጠኝነት ገንቢ ስራ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ዜጎች ላይ ተስፋን የሚጭሩ እና ብርሃን የሚያሳዩ መሆን እንዳለባቸውም ተናግረዋል። ድልድይ ሰዎችን እንደሚያገናኘው ሁሉ ትርክት የሰዎችን አዕምሮ ያገናኛል ያሉት ፕሬዝዳንቱ መገናኛ ብዙሃና የጋራ ትርክት ላይ በማተኮር ሀገር እና መንግስት ተቀራርበው እንዲሰሩ ምቹ መደላልድል መፍጠር እንደሚገባቸው አንስተዋል። ዘመን ተሻጋሪ የሚሆኑ ትርክቶችን በመቅረጽ፣ የህዝብ ድምጽ በመሆን እና ተቋማትን በማጠናከር ረገድ ጋዜጠኞች ወሳኝ ሚና አላቸው ብለዋል።   በተለይም ዜጎችን ትክክለኛ እና እውነተኛ መረጃ በማስታጠቅ እና ንቃተ ህሊናቸውን በማሳደግ ለሀገራቸው ጥቅም እና ፍላጎት እንዲቆሙ የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ነው ያሉት። ጋዜጠኛው ለፈተናዎች እና ለችግሮች እጅ ሳይሰጥ በአይበገሬነት በመስራት ሀገርን የሚገነቡ እና ትውልድን የሚቀርጹ ስራዎችን ማከናወን እንዳለባት አሳስበዋል።
ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎችና መራጮች ምዝገባ በቴክኖሎጂ ታግዞ እንዲካሄድ የሚያስችል አሰራር ተዘጋጅቷል
Jul 16, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ለሰባተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎችና መራጮች ምዝገባ በምርጫ ጣቢያዎች በአካል ተገኝተው ከማካሄድ በተጨማሪ በቴክኖሎጂ ጭምር እንዲካሄድ አሰራር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ቦርዱ የምርጫ ጣቢያዎች ስያሜዎች ደረጃቸውን የጠበቁና ወጥነት ያላቸው እንዲሆኑም እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለማካሄድ የተለያዩ ዝግጅቶችን እያደረገ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት ሰባተኛው ዙር አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ከቀደሙት ምርጫዎች በተሻለ መልኩ ለማካሄድ ከህግ-ማሻሻል ጨምሮ ሌሎች ዝግጅቶች እየተደረጉ ናቸው። በፖለቲካ ፓርቲዎች አስተዳደርና የምርጫ ስርዓት ማስፈጸሚያ አዋጅ ላይ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ጥናት መካሄዱንም ነው ያነሱት። ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች ሲካሄድ የነበረው የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ጭምር እንዲካሄድም አሰራር መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እንደእርሳቸው ገለጻ፤ የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ በምርጫ ጣቢያ በአካል ተገኝተው ከመመዝገብ በተጨማሪ ስማርት ስልክና ታብሌትን በመሳሰሉ ቴክኖሎጂዎች ለማካሄድ አማራጮች ተዘጋጅተዋል። የማሻሻያ አዋጁ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን አካቶ እንዲፀድቅም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን አስታውቀዋል። የምርጫ ጣቢያዎችን ለመራጮች ምቹና ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ የምርጫ ጣቢያዎች ስያሜ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲሰየም ዝግጅቶች መደረጋቸውን ነው ሰብሳቢዋ የተናገሩት። በዚህም የምርጫ ጣቢያዎችን የማደራጀት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በእያንዳንዱ ምርጫ ጣቢያ መሰረተ ልማትና ግብዓት የማሟላት ሥራ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። ቦርዱ በአገራዊ ምርጫው ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲያዝ እየሰራ መሆኑን ነው ሰብሳቢዋ የገለጹት። የፖለቲካ ፓርቲዎች መርሃ ግብሮቻቸውን ለመራጩ ህዝብ በተገቢው መንገድ እንዲያቀርቡ በቂ ስልጠና መስጠቱንም እንዲሁ። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመረጃ ላይ የተመሰረተ መራጭ እንዲኖራቸው መርሃ ግብሮቻቸውን የሚያስተዋውቁበት ይፋዊ መድረክ በቅርቡ እንደሚጀምሩም ጠቁመዋል።  
ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች ተካሒደዋል
Jul 16, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች ማካሄዱን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጻም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አቅጣጫ ላይ ግምገማዊ ውይይት ማካሄዱን አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ለኢዜአ የላከው መግለጫ አመልክቷል። የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ስትራቴጂክ አመራሮች በተገኙበት መድረክ በተካሄደው ውይይት በ2017 በጀት ዓመት ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊና ቀጣናዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ጫናዎችን በመቋቋም ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች እና የኦፕሬሽን ሥራዎች መከናወናቸው በመግለጫው ተጠቁሟል። በበጀት ዓመቱ ተቋሙ የተሰጠውን መረጃ የመሰብሰብና የመተንተን ተልዕኮ ከመወጣት አንፃር ስትራቴጂክ፣ ኦፕሬሽናልና ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎችን በማመንጨት ለውሳኔ ሰጪ አካላት ግብዓት እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል።   የተሰበሰቡ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ከሌሎች የፀጥታና መረጃ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የሕግ የበላይነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን የሚያስችሉ የኦፕሬሽን ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለያዩ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች የተሳተፉና ከብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅም በተጻራሪ የተሰለፉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል። ይህን ተከትሎም አሁን ላይ በአንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች የነበሩ የፀጥታ ችግሮች እየተፈቱ መሠረታዊ መሻሻሎች ታይተዋል። በሀገሪቱ የተካሄዱ በርካታ ዓለም-አቀፍና አህጉራዊ ጉባኤዎችን እንዲሁም የአቪዬሽን ደኅንነትን በማረጋገጥ ረገድ ምንም አይነት ክፍተት እንይፈጠር አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ውጤታማ ስምሪት ማካሄዱን መግለጫው አመልክቷል።   አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የሥነ- ልቦና ጦርነትን ለመምራት እና ለማስተባበር በሕግ የተሰጠውን ኃላፊነት መሰረት አድርጎ ከውስጥ እና ከውጭ ሀገራችንን እና የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም ብሔራዊ ደኅንነትን ኢላማ አድርገው የተቃጡ ጦርነቶችን የመመከት፣ የመከላከል እና አስፈላጊ ሲሆንም የማጥቃት እርምጃዎችን በመውሰድ ረገድ ስኬታማ ተግባር ማከናወኑ በመግለጫው ተጠቅሷል። በበጀት ዓመቱ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ባከናወናቸው ሥራዎች እንደ ተቋም መረጃን የመሰብሰብ፤ የመተንተን እና የመመዘን አቅምን ማሳደግ የተቻለበት፤ ብሔራዊ ጥቅምን ሊያስጠብቁ የሚያስችሉ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ስምሪቶች የተከናወኑበት፤ ቴክኖሎጂን መታጠቅ ብቻ ሳይሆን በራስ አቅም ማላመድና ማበልፀግ ላይ ውጤት የተገኘበት እንዲሁም ሀብትን አቀናጅቶ መጠቀም ልምድ የዳበረበት መሆኑ እንደ ጥንካሬ ተነስቷል።   ባለፉት ዓመታት ትኩረት ተሰጥቷቸው በተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች በአሰራር ስርዓት የዘመነ፤ የሰለጠነ የሰው ኃይል የያዘና ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ የታጠቀ እንዲሁም ኢትዮጵያን የሚመስል ተቋም ለመገንባት የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት እንደነበር ተገምግሟል። የመረጃና ደኅንነት ስምሪት ከተለዋዋጭ ሁኔታዎች ጋር ተጣጥሞ መካሄድ ስላለበት በቀጣይ የሪፎርም አጀንዳዎችን መከለስና ወቅቱን የሚዋጁ አዳዲስ አቅጣጫዎችን መስቀመጥ እንደሚገባ በመድረኩ ተጠቁሟል። በሚቀጥለው ዓመትም የሀገሪቱን የፀጥታ ሁኔታ ሙሉ ለሙሉ ወደ ተሟላ ሰላምና መረጋጋት መለወጥ፤ ለሀገራዊ ምርጫ ምቹ መደላድልን መፍጠር፤ ተለዋዋጭ ለሆኑ ሁኔታዎች ስትራቴጂካዊ ዝግጁነትን ማጠናከር ዋናዎቹ የትኩረት አቅጣጫ መሆናቸው ተነስቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በቀጣይ ዓመት እንደ ሀገር የሚከወኑ ሁነቶችን ተከትሎ ከውስጥና ከውጭ የሚሰነዘሩ የደኅንነት ስጋቶችን መቀልበስ የሚያስችል የሰው ኃይል፣ የቴክኖሎጂና የሎጀስቲክስ ቁመና ላይ እንደሚገኝ በመድረኩ መገምገሙን አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አስታውቋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
መገናኛ ብዙሃን ሀገርን የሚገነቡ ተሻጋሪ ትርክቶች ላይ በትኩረት መስራት አለባቸው - አቶ ዛዲግ አብርሃ
Jul 16, 2025 103
  አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ሀገርን የሚገነቡ ዘመን ተሻጋሪ ትርክቶችን የመቅረጽ ሚናቸውን በተገቢው ሁኔታ መወጣት እንዳለባቸው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለጹ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት(ኢዜአ) አመራሮች እና ጋዜጠኞች ስልጠና እየሰጡ ይገኛል። አቶ ዛዲግ መገናኛ ብዙሃን መረጃን ከማቅረብ ባሻገር መሰረታዊ ለውጥን የሚያመጡ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባቸው ገልጸዋል። በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን ሀገርን ለመገንባትና ዜጎችንም ለጋራ ሀገራዊ ግብ በአንድነት እንዲቆሙ የሚያስችሉ የይዘት ስራዎች ላይ ማተኮር አለባቸው ብለዋል።   መገናኛ ብዙሃን ለሀገር ግንባታ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን ጠቅሰው የግንባታ ሂደቱን ከማሳለጥ አኳያ ገንቢ ሚና መጫወት እንዳለባቸው አንስተዋል። ጋዜጠኞችም ከዕለት ደራሽ ዜና ባለፈ አዎንታዊ ተጽእኖ የሚፈጥር ይዘት ሰርቻለሁ ወይ? በሚል ራሳቸውን በመፈተሽ ዘላቂነት ላላቸው ጉዳዮች ትኩረት መስጠትና ራሳቸውን ማብቃት እንደሚኖርባቸው አመልክተዋል። መገናኛ ብዙሃን ችግር ነቃሽ ብቻ ሳይሆኑ መፍትሄ አፍላቂ መሆን ይገባቸዋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለዚህም የጋዜጠኝነት ገንቢ ስራ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ዜጎች ላይ ተስፋን የሚጭሩ እና ብርሃን የሚያሳዩ መሆን እንዳለባቸውም ተናግረዋል። ድልድይ ሰዎችን እንደሚያገናኘው ሁሉ ትርክት የሰዎችን አዕምሮ ያገናኛል ያሉት ፕሬዝዳንቱ መገናኛ ብዙሃና የጋራ ትርክት ላይ በማተኮር ሀገር እና መንግስት ተቀራርበው እንዲሰሩ ምቹ መደላልድል መፍጠር እንደሚገባቸው አንስተዋል። ዘመን ተሻጋሪ የሚሆኑ ትርክቶችን በመቅረጽ፣ የህዝብ ድምጽ በመሆን እና ተቋማትን በማጠናከር ረገድ ጋዜጠኞች ወሳኝ ሚና አላቸው ብለዋል።   በተለይም ዜጎችን ትክክለኛ እና እውነተኛ መረጃ በማስታጠቅ እና ንቃተ ህሊናቸውን በማሳደግ ለሀገራቸው ጥቅም እና ፍላጎት እንዲቆሙ የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ነው ያሉት። ጋዜጠኛው ለፈተናዎች እና ለችግሮች እጅ ሳይሰጥ በአይበገሬነት በመስራት ሀገርን የሚገነቡ እና ትውልድን የሚቀርጹ ስራዎችን ማከናወን እንዳለባት አሳስበዋል።
ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎችና መራጮች ምዝገባ በቴክኖሎጂ ታግዞ እንዲካሄድ የሚያስችል አሰራር ተዘጋጅቷል
Jul 16, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ለሰባተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎችና መራጮች ምዝገባ በምርጫ ጣቢያዎች በአካል ተገኝተው ከማካሄድ በተጨማሪ በቴክኖሎጂ ጭምር እንዲካሄድ አሰራር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ቦርዱ የምርጫ ጣቢያዎች ስያሜዎች ደረጃቸውን የጠበቁና ወጥነት ያላቸው እንዲሆኑም እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለማካሄድ የተለያዩ ዝግጅቶችን እያደረገ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት ሰባተኛው ዙር አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ከቀደሙት ምርጫዎች በተሻለ መልኩ ለማካሄድ ከህግ-ማሻሻል ጨምሮ ሌሎች ዝግጅቶች እየተደረጉ ናቸው። በፖለቲካ ፓርቲዎች አስተዳደርና የምርጫ ስርዓት ማስፈጸሚያ አዋጅ ላይ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ጥናት መካሄዱንም ነው ያነሱት። ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች ሲካሄድ የነበረው የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ጭምር እንዲካሄድም አሰራር መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እንደእርሳቸው ገለጻ፤ የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ በምርጫ ጣቢያ በአካል ተገኝተው ከመመዝገብ በተጨማሪ ስማርት ስልክና ታብሌትን በመሳሰሉ ቴክኖሎጂዎች ለማካሄድ አማራጮች ተዘጋጅተዋል። የማሻሻያ አዋጁ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን አካቶ እንዲፀድቅም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን አስታውቀዋል። የምርጫ ጣቢያዎችን ለመራጮች ምቹና ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ የምርጫ ጣቢያዎች ስያሜ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲሰየም ዝግጅቶች መደረጋቸውን ነው ሰብሳቢዋ የተናገሩት። በዚህም የምርጫ ጣቢያዎችን የማደራጀት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በእያንዳንዱ ምርጫ ጣቢያ መሰረተ ልማትና ግብዓት የማሟላት ሥራ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። ቦርዱ በአገራዊ ምርጫው ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲያዝ እየሰራ መሆኑን ነው ሰብሳቢዋ የገለጹት። የፖለቲካ ፓርቲዎች መርሃ ግብሮቻቸውን ለመራጩ ህዝብ በተገቢው መንገድ እንዲያቀርቡ በቂ ስልጠና መስጠቱንም እንዲሁ። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመረጃ ላይ የተመሰረተ መራጭ እንዲኖራቸው መርሃ ግብሮቻቸውን የሚያስተዋውቁበት ይፋዊ መድረክ በቅርቡ እንደሚጀምሩም ጠቁመዋል።  
ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች ተካሒደዋል
Jul 16, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች ማካሄዱን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጻም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አቅጣጫ ላይ ግምገማዊ ውይይት ማካሄዱን አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ለኢዜአ የላከው መግለጫ አመልክቷል። የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ስትራቴጂክ አመራሮች በተገኙበት መድረክ በተካሄደው ውይይት በ2017 በጀት ዓመት ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊና ቀጣናዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ጫናዎችን በመቋቋም ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች እና የኦፕሬሽን ሥራዎች መከናወናቸው በመግለጫው ተጠቁሟል። በበጀት ዓመቱ ተቋሙ የተሰጠውን መረጃ የመሰብሰብና የመተንተን ተልዕኮ ከመወጣት አንፃር ስትራቴጂክ፣ ኦፕሬሽናልና ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎችን በማመንጨት ለውሳኔ ሰጪ አካላት ግብዓት እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል።   የተሰበሰቡ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ከሌሎች የፀጥታና መረጃ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የሕግ የበላይነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን የሚያስችሉ የኦፕሬሽን ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለያዩ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች የተሳተፉና ከብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅም በተጻራሪ የተሰለፉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል። ይህን ተከትሎም አሁን ላይ በአንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች የነበሩ የፀጥታ ችግሮች እየተፈቱ መሠረታዊ መሻሻሎች ታይተዋል። በሀገሪቱ የተካሄዱ በርካታ ዓለም-አቀፍና አህጉራዊ ጉባኤዎችን እንዲሁም የአቪዬሽን ደኅንነትን በማረጋገጥ ረገድ ምንም አይነት ክፍተት እንይፈጠር አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ውጤታማ ስምሪት ማካሄዱን መግለጫው አመልክቷል።   አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የሥነ- ልቦና ጦርነትን ለመምራት እና ለማስተባበር በሕግ የተሰጠውን ኃላፊነት መሰረት አድርጎ ከውስጥ እና ከውጭ ሀገራችንን እና የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም ብሔራዊ ደኅንነትን ኢላማ አድርገው የተቃጡ ጦርነቶችን የመመከት፣ የመከላከል እና አስፈላጊ ሲሆንም የማጥቃት እርምጃዎችን በመውሰድ ረገድ ስኬታማ ተግባር ማከናወኑ በመግለጫው ተጠቅሷል። በበጀት ዓመቱ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ባከናወናቸው ሥራዎች እንደ ተቋም መረጃን የመሰብሰብ፤ የመተንተን እና የመመዘን አቅምን ማሳደግ የተቻለበት፤ ብሔራዊ ጥቅምን ሊያስጠብቁ የሚያስችሉ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ስምሪቶች የተከናወኑበት፤ ቴክኖሎጂን መታጠቅ ብቻ ሳይሆን በራስ አቅም ማላመድና ማበልፀግ ላይ ውጤት የተገኘበት እንዲሁም ሀብትን አቀናጅቶ መጠቀም ልምድ የዳበረበት መሆኑ እንደ ጥንካሬ ተነስቷል።   ባለፉት ዓመታት ትኩረት ተሰጥቷቸው በተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች በአሰራር ስርዓት የዘመነ፤ የሰለጠነ የሰው ኃይል የያዘና ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ የታጠቀ እንዲሁም ኢትዮጵያን የሚመስል ተቋም ለመገንባት የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት እንደነበር ተገምግሟል። የመረጃና ደኅንነት ስምሪት ከተለዋዋጭ ሁኔታዎች ጋር ተጣጥሞ መካሄድ ስላለበት በቀጣይ የሪፎርም አጀንዳዎችን መከለስና ወቅቱን የሚዋጁ አዳዲስ አቅጣጫዎችን መስቀመጥ እንደሚገባ በመድረኩ ተጠቁሟል። በሚቀጥለው ዓመትም የሀገሪቱን የፀጥታ ሁኔታ ሙሉ ለሙሉ ወደ ተሟላ ሰላምና መረጋጋት መለወጥ፤ ለሀገራዊ ምርጫ ምቹ መደላድልን መፍጠር፤ ተለዋዋጭ ለሆኑ ሁኔታዎች ስትራቴጂካዊ ዝግጁነትን ማጠናከር ዋናዎቹ የትኩረት አቅጣጫ መሆናቸው ተነስቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በቀጣይ ዓመት እንደ ሀገር የሚከወኑ ሁነቶችን ተከትሎ ከውስጥና ከውጭ የሚሰነዘሩ የደኅንነት ስጋቶችን መቀልበስ የሚያስችል የሰው ኃይል፣ የቴክኖሎጂና የሎጀስቲክስ ቁመና ላይ እንደሚገኝ በመድረኩ መገምገሙን አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አስታውቋል።
‎የሲዳማ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ አዋጆችን እና ሹመት በማፅደቅ ተጠናቀቀ
Jul 16, 2025 61
‎ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ) ፡- የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን የተለያዩ አዋጆችን እና ሹመት በማፅደቅ አጠናቀቀ ። ምክር ቤቱ የቀረበለትን የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል ። ‎አዋጁ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የተሰጣቸውን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጡ፣ በሰራተኞች መካከል ፍትሀዊና አዎንታዊ ውድድር እንዲኖር ሚና ያለው እንደሆነ ተገልጿል ።   ‎በሌላ በኩል የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስፈፃሚ አካላት ማቋቋሚያ ፤ ሥልጣንና ተግባር መወሰኛ ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል ። ‎አዋጁ በሀገርና በክልል ደረጃ ያለውን ለውጥ መነሻ በማድረግ ተቋማት ለህብረተሰቡ የሚሰጡት አገልግሎቶች ተደራሽና አካታች እንዲሆኑ ብሎም ተግባራቸውን በቅንጅት እንዲፈፅሙና ሀብትን በአግባቡ መጠቀም እንዲችሉ ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተጠቅሷል ። ‎ምክር ቤቱ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አደረጃጀት ሥልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣ ረቂቅ አዋጅንም እንዲሁ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል ። ይህም ፖሊስ የተሰጠውን ሕገመንግስታዊ ተልዕኮውን በብቃት እንዲወጣ የሚያስችለው እንደሆነ ተጠቁሟል። ‎በተጨማሪም የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሀዋሳ ከተማ መዋቅራዊ የውስጥ አደረጃጀትን መልሶ ለማዋቀር የቀረበውን ረቂቅ አዋጅም አፅድቋል ። ‎በዚህም የሀዋሳ ከተማ በአምስት ክፍለ ከተሞችና 26 ቀበሌዎች የሚዋቀር መሆኑ ተመለክቷል። ምክር ቤቱ የቀረቡለትን የተለያዩ ሹመቶችን አፅድቋል ። በዚህም መሰረት ፡- 1/አቶ ቢኒያም ሰለሞንን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ፣ 2/አቶ ገነነ ሹኔን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ፣ 3/ አቶ ፍቅረየሱስ አሸናፊን የክልሉ የመሬት አስተዳደርና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ 4/ አቶ ዳዊት ዳንጊሶን የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አድርጎ የሾመ ሲሆን፤ ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ አባላት ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈፅመዋል ።የምክር ቤቱ ጉባኤ መረሃ ግብሩን በዚሁ አጠናቋል።
በራስ ፀጋ የምግብ ሉዓላዊነትን እና ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል
Jul 16, 2025 98
ድሬደዋ፣ ሐምሌ 09/2017(ኢዜአ ) በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በራስ ፀጋ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ገለጹ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬደዋ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ የብልፅግና ፓርቲ ዋና መስሪያ ቤት እና የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አመራሮች፣ ሚኒስትሮች እና የየክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።   ከተረጅነት የመውጣት ጥረት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን በመቀነስ ረገድና ሌሎችም ጉዳዮችን በመዳሰስ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና የተመዘገቡ ውጤቶችን በተመለከተ በስፋት ውይይት ተደርጓል።   በዚሁ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፤ ለዜጎች በውጭና ሀገር ውስጥ የስራ እድል በማመቻቸትና በመፍጠር ረገድ የተሳካ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። በኢትዮጵያ ክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ እንዲኖር በማድረግ ዜጎች በቀሰሙት ዕውቀትና ክህሎት ለሀገር ከፍታና ብልፅግና መረጋገጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ከስራ እድል ፈጠራም ባለፈ በሌሎች ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተው በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተረጂነት ለመውጣት እና በራስ ፀጋ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በፓርቲና በመንግስት ትብብር የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን አንስተዋል። በመሆኑም የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል በተያዘው በጀት ዓመትም የላቀ አፈፃፀም እንዲኖር የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።   የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ(ዶ/ር)፤ በበኩላቸው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ የሀገሪቱን ዘርፈ ብዙ ልማትና እድገት ማሳለጥ መቻሉን አንስተዋል።   የገበያ መረጋጋት እንዲኖር በመስራት የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት ረገድ በስፋት ጥረት መደረጉንም ተናግረዋል።
በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገቡ ስኬቶችን ህዝብን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Jul 15, 2025 140
አዳማ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፦ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገቡ ስኬቶችን ህዝብን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልል የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና መዋቅሮች እውቅና ተሰጥቷል። እውቅናው የተሰጠው ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ በቆየው የ2017 ዓ/ም የፓርቲና የመንግስት የስራ አፈፃፀም እና የ2018 ዓ/ም እቅድ አቅጣጫ የግምገማ መድረክ ማምሻውን ሲጠናቀቅ ነው። በወቅቱ አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዳሉት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም መስክ በሚባል ደረጃ ስኬታማ ስራ ማከናወን ተችሏል። ይህንን ጥንካሬ ለማስቀጠል በግምገማው የጥንካሬ እና የድክመት መንስኤዎችን በጥልቀት መርምረን በመለየት አቅጣጫ አስቀምጠናል ብለዋል።   በመሆኑም በአዲሱ በጀት ዓመት የጥንካሬ መሠረቶችን በማስፋት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረው እንቅስቃሴ በየደረጃው ያለው አመራር በተነሳሽነትና በቁርጠኝነት ለመስራት እንዲዘጋጅ አሳስበዋል። እውቅናና ሽልማት ላገኙ መዋቅሮች የእንኳን ደስ አላችሁ በማለትም ባገኛችሁት ስኬት ሳትኩራሩ፣ ለበለጠ እንድትተጉ ሲሉ አስገንዝበዋል።   የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ በበኩላቸው በክልሉ መንግስት ሽልማትና እውቅና የተሰጠው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ስራን በጥራትና በብዛት መፈፀም የቻሉ አካላትን ለማበረታታት ነው ብለዋል። በተለይ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በሁሉም የልማት መስኮች፣ በፀጥታና በመልካም አስተዳደር፣ በገቢ አሰባሰብና በተለያዩ ኢኒሼቲቮች ህብረተሰቡን በተጨባጭ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። ዞኖች፣ ወረዳዎች፣ ከተሞችና ቀበሌዎች ካላቸው መዋቅራዊ አደረጃጀት አኳያ እርስ በእርሰ እንዲወዳደሩ ጥረት መደረጉንም ገልፀዋል። እውቅናና ሽልማቱ የተሻለ የሰሩትን ለማበረታታትና የአፈፃፀም ክፍተት ያለባቸው ደግሞ እንዲያስተካክሉ ማድረግን ያለመ ነው ብለዋል። በመሆኑም በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የገጠርና የከተማ ቀበሌዎችና ወረዳዎች፣ ዞኖች፣ ለከተሞችና የክልል ሴክተሮች እውቅናና ሽልማት መሰጠቱን አመልክተዋል። ይህም እውቅና በየደረጃው የህዝብን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ጠንካራ መዋቅር ለመገንባት መነሳሳትንና የውድድር መንፈስን ለማጎልበት ያስችላል ነው ያሉት።
ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ
Jul 15, 2025 241
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፦ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፤ በፑንትላንድ የሚንቀሳቀሰው የአይ ኤስ የሶማሊያ ክንፍ በተለያዩ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ለመስፋፋትና የሽብር ቡድኑን ሴሎች ለመመስረት የሚያደርገውን ጥረት በተመለከተ የመረጃ ስምሪትና ጥናት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ የአይ ኤስ የሶማሊያ ክንፍ በኢትዮጵያ የሽብር መረብ ለመዘርጋት የሚያደርገውን ሙከራ በተመለከተ ከጅምሩ በመረጃና በማስረጃ ተደግፎ ጥብቅ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን በመግለጫው ያስታወቀው አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ፤ የሥጋት ደረጃውን በተመለከተ በየጊዜው ባከናወነው ግምገማ ተጋላጭነትን የሚያስከትሉና ወደ ብሔራዊ ደኅንነት ሥጋት የሚያድጉ ተጨባጭ ግኝቶች መለየታቸውን ጠቁሟል፡፡ እንደ መግለጫው፤ የተከናወነውን ተጨባጭ መረጃና ማስረጃ የማጠናቀር ሂደት ተከትሎ የሽብር ቡድኑ በፑንትላንድ አሰልጥኖ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያሰማራቸው 82 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከፌዴራል ፖሊስና ከክልል የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ከቡድኑ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸውና ሁለንተናዊ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች መካተታቸውን በመግለጽ፤ በተለይ በዓለም-አቀፍ የሽብር ቡድኑ በመረጃ ክንፍ የተደራጁ እንዲሁም በፋይናንስና በሎጀስቲክ እገዛ ሲያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው በመግለጫው ተመላክቷል፡፡ የሽብር ቡድኑ የጥፋት ተልዕኮውን ለማስፋፋትና ምልመላ ለማከናወን የሃይማኖት ተቋማትንና ሃይማኖትን እንደ ሽፋን ይጠቀማል ያለው የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መግለጫ፤ የሕዝብን አንድነትና ተከባብሮ የመኖር እሴት የሚሸረሽሩ ብሎም ለአመጽና ሁከት የሚያነሳሱ አስተምህሮዎችን ለማስፋፋት ሙከራ ሲደረግ እንደነበር በተጨባጭ ማስረጃ መረጋገጡን አስታውቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ፣ አዳማ፣ ሃሮማያ፣ ሻሸመኔ፣ ባሌ፣ ጅማና ሻኪሶ ከተማ ዙሪያ፤ በአማራ ክልል ከሚሴ አካባቢ፤ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞንና ሃላባ ቁሊቶ ከተማ፤ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማና በሐረሪ ክልል በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፤ ግለሰቦቹን ለመያዝ በተደረገው ስምሪት በየአካባቢው የሚገኘው ኅብረተሰብ ከደኅንነትና ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ያሳየው ተሳትፎ በመልካም አርዓያነት የሚጠቀስ እንደነበር የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መግለጫ ጠቁሟል፡፡ በቁጥጥር ስር ያልዋሉ የሽብር ቡድኑ አባላት ላይ የሚደረገው ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያመለከተው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ኅብረተሰቡም በየአካባቢው ሰላምን የሚያደፈርሱና ስጋት ሊፈጥሩ የሚችሉ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት አንደ ሁልጊዜው ለሚመለከታቸው የደኅንነትና የጸጥታ አካላት ጥቆማ በማቅረብ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ፖለቲካ
መገናኛ ብዙሃን ሀገርን የሚገነቡ ተሻጋሪ ትርክቶች ላይ በትኩረት መስራት አለባቸው - አቶ ዛዲግ አብርሃ
Jul 16, 2025 103
  አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ሀገርን የሚገነቡ ዘመን ተሻጋሪ ትርክቶችን የመቅረጽ ሚናቸውን በተገቢው ሁኔታ መወጣት እንዳለባቸው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለጹ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት(ኢዜአ) አመራሮች እና ጋዜጠኞች ስልጠና እየሰጡ ይገኛል። አቶ ዛዲግ መገናኛ ብዙሃን መረጃን ከማቅረብ ባሻገር መሰረታዊ ለውጥን የሚያመጡ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባቸው ገልጸዋል። በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን ሀገርን ለመገንባትና ዜጎችንም ለጋራ ሀገራዊ ግብ በአንድነት እንዲቆሙ የሚያስችሉ የይዘት ስራዎች ላይ ማተኮር አለባቸው ብለዋል።   መገናኛ ብዙሃን ለሀገር ግንባታ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን ጠቅሰው የግንባታ ሂደቱን ከማሳለጥ አኳያ ገንቢ ሚና መጫወት እንዳለባቸው አንስተዋል። ጋዜጠኞችም ከዕለት ደራሽ ዜና ባለፈ አዎንታዊ ተጽእኖ የሚፈጥር ይዘት ሰርቻለሁ ወይ? በሚል ራሳቸውን በመፈተሽ ዘላቂነት ላላቸው ጉዳዮች ትኩረት መስጠትና ራሳቸውን ማብቃት እንደሚኖርባቸው አመልክተዋል። መገናኛ ብዙሃን ችግር ነቃሽ ብቻ ሳይሆኑ መፍትሄ አፍላቂ መሆን ይገባቸዋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለዚህም የጋዜጠኝነት ገንቢ ስራ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ዜጎች ላይ ተስፋን የሚጭሩ እና ብርሃን የሚያሳዩ መሆን እንዳለባቸውም ተናግረዋል። ድልድይ ሰዎችን እንደሚያገናኘው ሁሉ ትርክት የሰዎችን አዕምሮ ያገናኛል ያሉት ፕሬዝዳንቱ መገናኛ ብዙሃና የጋራ ትርክት ላይ በማተኮር ሀገር እና መንግስት ተቀራርበው እንዲሰሩ ምቹ መደላልድል መፍጠር እንደሚገባቸው አንስተዋል። ዘመን ተሻጋሪ የሚሆኑ ትርክቶችን በመቅረጽ፣ የህዝብ ድምጽ በመሆን እና ተቋማትን በማጠናከር ረገድ ጋዜጠኞች ወሳኝ ሚና አላቸው ብለዋል።   በተለይም ዜጎችን ትክክለኛ እና እውነተኛ መረጃ በማስታጠቅ እና ንቃተ ህሊናቸውን በማሳደግ ለሀገራቸው ጥቅም እና ፍላጎት እንዲቆሙ የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ነው ያሉት። ጋዜጠኛው ለፈተናዎች እና ለችግሮች እጅ ሳይሰጥ በአይበገሬነት በመስራት ሀገርን የሚገነቡ እና ትውልድን የሚቀርጹ ስራዎችን ማከናወን እንዳለባት አሳስበዋል።
ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎችና መራጮች ምዝገባ በቴክኖሎጂ ታግዞ እንዲካሄድ የሚያስችል አሰራር ተዘጋጅቷል
Jul 16, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ለሰባተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎችና መራጮች ምዝገባ በምርጫ ጣቢያዎች በአካል ተገኝተው ከማካሄድ በተጨማሪ በቴክኖሎጂ ጭምር እንዲካሄድ አሰራር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ቦርዱ የምርጫ ጣቢያዎች ስያሜዎች ደረጃቸውን የጠበቁና ወጥነት ያላቸው እንዲሆኑም እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለማካሄድ የተለያዩ ዝግጅቶችን እያደረገ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት ሰባተኛው ዙር አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ከቀደሙት ምርጫዎች በተሻለ መልኩ ለማካሄድ ከህግ-ማሻሻል ጨምሮ ሌሎች ዝግጅቶች እየተደረጉ ናቸው። በፖለቲካ ፓርቲዎች አስተዳደርና የምርጫ ስርዓት ማስፈጸሚያ አዋጅ ላይ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ጥናት መካሄዱንም ነው ያነሱት። ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች ሲካሄድ የነበረው የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ጭምር እንዲካሄድም አሰራር መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እንደእርሳቸው ገለጻ፤ የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ በምርጫ ጣቢያ በአካል ተገኝተው ከመመዝገብ በተጨማሪ ስማርት ስልክና ታብሌትን በመሳሰሉ ቴክኖሎጂዎች ለማካሄድ አማራጮች ተዘጋጅተዋል። የማሻሻያ አዋጁ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን አካቶ እንዲፀድቅም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን አስታውቀዋል። የምርጫ ጣቢያዎችን ለመራጮች ምቹና ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ የምርጫ ጣቢያዎች ስያሜ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲሰየም ዝግጅቶች መደረጋቸውን ነው ሰብሳቢዋ የተናገሩት። በዚህም የምርጫ ጣቢያዎችን የማደራጀት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በእያንዳንዱ ምርጫ ጣቢያ መሰረተ ልማትና ግብዓት የማሟላት ሥራ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። ቦርዱ በአገራዊ ምርጫው ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲያዝ እየሰራ መሆኑን ነው ሰብሳቢዋ የገለጹት። የፖለቲካ ፓርቲዎች መርሃ ግብሮቻቸውን ለመራጩ ህዝብ በተገቢው መንገድ እንዲያቀርቡ በቂ ስልጠና መስጠቱንም እንዲሁ። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመረጃ ላይ የተመሰረተ መራጭ እንዲኖራቸው መርሃ ግብሮቻቸውን የሚያስተዋውቁበት ይፋዊ መድረክ በቅርቡ እንደሚጀምሩም ጠቁመዋል።  
ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች ተካሒደዋል
Jul 16, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች ማካሄዱን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጻም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አቅጣጫ ላይ ግምገማዊ ውይይት ማካሄዱን አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ለኢዜአ የላከው መግለጫ አመልክቷል። የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ስትራቴጂክ አመራሮች በተገኙበት መድረክ በተካሄደው ውይይት በ2017 በጀት ዓመት ተለዋዋጭና ኢተገማች በሆነ ዓለም-ዓቀፋዊና ቀጣናዊ የደኅንነት አውድ ውስጥ ጫናዎችን በመቋቋም ሀገርን ማፅናት ያስቻሉ ስምሪቶች እና የኦፕሬሽን ሥራዎች መከናወናቸው በመግለጫው ተጠቁሟል። በበጀት ዓመቱ ተቋሙ የተሰጠውን መረጃ የመሰብሰብና የመተንተን ተልዕኮ ከመወጣት አንፃር ስትራቴጂክ፣ ኦፕሬሽናልና ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎችን በማመንጨት ለውሳኔ ሰጪ አካላት ግብዓት እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል።   የተሰበሰቡ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ከሌሎች የፀጥታና መረጃ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የሕግ የበላይነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን የሚያስችሉ የኦፕሬሽን ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለያዩ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች የተሳተፉና ከብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅም በተጻራሪ የተሰለፉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል። ይህን ተከትሎም አሁን ላይ በአንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች የነበሩ የፀጥታ ችግሮች እየተፈቱ መሠረታዊ መሻሻሎች ታይተዋል። በሀገሪቱ የተካሄዱ በርካታ ዓለም-አቀፍና አህጉራዊ ጉባኤዎችን እንዲሁም የአቪዬሽን ደኅንነትን በማረጋገጥ ረገድ ምንም አይነት ክፍተት እንይፈጠር አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ውጤታማ ስምሪት ማካሄዱን መግለጫው አመልክቷል።   አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የሥነ- ልቦና ጦርነትን ለመምራት እና ለማስተባበር በሕግ የተሰጠውን ኃላፊነት መሰረት አድርጎ ከውስጥ እና ከውጭ ሀገራችንን እና የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም ብሔራዊ ደኅንነትን ኢላማ አድርገው የተቃጡ ጦርነቶችን የመመከት፣ የመከላከል እና አስፈላጊ ሲሆንም የማጥቃት እርምጃዎችን በመውሰድ ረገድ ስኬታማ ተግባር ማከናወኑ በመግለጫው ተጠቅሷል። በበጀት ዓመቱ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ባከናወናቸው ሥራዎች እንደ ተቋም መረጃን የመሰብሰብ፤ የመተንተን እና የመመዘን አቅምን ማሳደግ የተቻለበት፤ ብሔራዊ ጥቅምን ሊያስጠብቁ የሚያስችሉ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ስምሪቶች የተከናወኑበት፤ ቴክኖሎጂን መታጠቅ ብቻ ሳይሆን በራስ አቅም ማላመድና ማበልፀግ ላይ ውጤት የተገኘበት እንዲሁም ሀብትን አቀናጅቶ መጠቀም ልምድ የዳበረበት መሆኑ እንደ ጥንካሬ ተነስቷል።   ባለፉት ዓመታት ትኩረት ተሰጥቷቸው በተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች በአሰራር ስርዓት የዘመነ፤ የሰለጠነ የሰው ኃይል የያዘና ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ የታጠቀ እንዲሁም ኢትዮጵያን የሚመስል ተቋም ለመገንባት የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት እንደነበር ተገምግሟል። የመረጃና ደኅንነት ስምሪት ከተለዋዋጭ ሁኔታዎች ጋር ተጣጥሞ መካሄድ ስላለበት በቀጣይ የሪፎርም አጀንዳዎችን መከለስና ወቅቱን የሚዋጁ አዳዲስ አቅጣጫዎችን መስቀመጥ እንደሚገባ በመድረኩ ተጠቁሟል። በሚቀጥለው ዓመትም የሀገሪቱን የፀጥታ ሁኔታ ሙሉ ለሙሉ ወደ ተሟላ ሰላምና መረጋጋት መለወጥ፤ ለሀገራዊ ምርጫ ምቹ መደላድልን መፍጠር፤ ተለዋዋጭ ለሆኑ ሁኔታዎች ስትራቴጂካዊ ዝግጁነትን ማጠናከር ዋናዎቹ የትኩረት አቅጣጫ መሆናቸው ተነስቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በቀጣይ ዓመት እንደ ሀገር የሚከወኑ ሁነቶችን ተከትሎ ከውስጥና ከውጭ የሚሰነዘሩ የደኅንነት ስጋቶችን መቀልበስ የሚያስችል የሰው ኃይል፣ የቴክኖሎጂና የሎጀስቲክስ ቁመና ላይ እንደሚገኝ በመድረኩ መገምገሙን አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አስታውቋል።
‎የሲዳማ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ አዋጆችን እና ሹመት በማፅደቅ ተጠናቀቀ
Jul 16, 2025 61
‎ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ) ፡- የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን የተለያዩ አዋጆችን እና ሹመት በማፅደቅ አጠናቀቀ ። ምክር ቤቱ የቀረበለትን የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል ። ‎አዋጁ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የተሰጣቸውን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጡ፣ በሰራተኞች መካከል ፍትሀዊና አዎንታዊ ውድድር እንዲኖር ሚና ያለው እንደሆነ ተገልጿል ።   ‎በሌላ በኩል የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስፈፃሚ አካላት ማቋቋሚያ ፤ ሥልጣንና ተግባር መወሰኛ ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል ። ‎አዋጁ በሀገርና በክልል ደረጃ ያለውን ለውጥ መነሻ በማድረግ ተቋማት ለህብረተሰቡ የሚሰጡት አገልግሎቶች ተደራሽና አካታች እንዲሆኑ ብሎም ተግባራቸውን በቅንጅት እንዲፈፅሙና ሀብትን በአግባቡ መጠቀም እንዲችሉ ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተጠቅሷል ። ‎ምክር ቤቱ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አደረጃጀት ሥልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣ ረቂቅ አዋጅንም እንዲሁ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል ። ይህም ፖሊስ የተሰጠውን ሕገመንግስታዊ ተልዕኮውን በብቃት እንዲወጣ የሚያስችለው እንደሆነ ተጠቁሟል። ‎በተጨማሪም የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሀዋሳ ከተማ መዋቅራዊ የውስጥ አደረጃጀትን መልሶ ለማዋቀር የቀረበውን ረቂቅ አዋጅም አፅድቋል ። ‎በዚህም የሀዋሳ ከተማ በአምስት ክፍለ ከተሞችና 26 ቀበሌዎች የሚዋቀር መሆኑ ተመለክቷል። ምክር ቤቱ የቀረቡለትን የተለያዩ ሹመቶችን አፅድቋል ። በዚህም መሰረት ፡- 1/አቶ ቢኒያም ሰለሞንን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ፣ 2/አቶ ገነነ ሹኔን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ፣ 3/ አቶ ፍቅረየሱስ አሸናፊን የክልሉ የመሬት አስተዳደርና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ 4/ አቶ ዳዊት ዳንጊሶን የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አድርጎ የሾመ ሲሆን፤ ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ አባላት ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈፅመዋል ።የምክር ቤቱ ጉባኤ መረሃ ግብሩን በዚሁ አጠናቋል።
በራስ ፀጋ የምግብ ሉዓላዊነትን እና ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል
Jul 16, 2025 98
ድሬደዋ፣ ሐምሌ 09/2017(ኢዜአ ) በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በራስ ፀጋ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ገለጹ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬደዋ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ የብልፅግና ፓርቲ ዋና መስሪያ ቤት እና የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አመራሮች፣ ሚኒስትሮች እና የየክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።   ከተረጅነት የመውጣት ጥረት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን በመቀነስ ረገድና ሌሎችም ጉዳዮችን በመዳሰስ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና የተመዘገቡ ውጤቶችን በተመለከተ በስፋት ውይይት ተደርጓል።   በዚሁ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፤ ለዜጎች በውጭና ሀገር ውስጥ የስራ እድል በማመቻቸትና በመፍጠር ረገድ የተሳካ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። በኢትዮጵያ ክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ እንዲኖር በማድረግ ዜጎች በቀሰሙት ዕውቀትና ክህሎት ለሀገር ከፍታና ብልፅግና መረጋገጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ከስራ እድል ፈጠራም ባለፈ በሌሎች ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተው በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተረጂነት ለመውጣት እና በራስ ፀጋ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በፓርቲና በመንግስት ትብብር የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን አንስተዋል። በመሆኑም የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል በተያዘው በጀት ዓመትም የላቀ አፈፃፀም እንዲኖር የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።   የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ(ዶ/ር)፤ በበኩላቸው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ የሀገሪቱን ዘርፈ ብዙ ልማትና እድገት ማሳለጥ መቻሉን አንስተዋል።   የገበያ መረጋጋት እንዲኖር በመስራት የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት ረገድ በስፋት ጥረት መደረጉንም ተናግረዋል።
በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገቡ ስኬቶችን ህዝብን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Jul 15, 2025 140
አዳማ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፦ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገቡ ስኬቶችን ህዝብን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ይበልጥ ለማጠናከር ይሰራል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልል የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና መዋቅሮች እውቅና ተሰጥቷል። እውቅናው የተሰጠው ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ በቆየው የ2017 ዓ/ም የፓርቲና የመንግስት የስራ አፈፃፀም እና የ2018 ዓ/ም እቅድ አቅጣጫ የግምገማ መድረክ ማምሻውን ሲጠናቀቅ ነው። በወቅቱ አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዳሉት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም መስክ በሚባል ደረጃ ስኬታማ ስራ ማከናወን ተችሏል። ይህንን ጥንካሬ ለማስቀጠል በግምገማው የጥንካሬ እና የድክመት መንስኤዎችን በጥልቀት መርምረን በመለየት አቅጣጫ አስቀምጠናል ብለዋል።   በመሆኑም በአዲሱ በጀት ዓመት የጥንካሬ መሠረቶችን በማስፋት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረው እንቅስቃሴ በየደረጃው ያለው አመራር በተነሳሽነትና በቁርጠኝነት ለመስራት እንዲዘጋጅ አሳስበዋል። እውቅናና ሽልማት ላገኙ መዋቅሮች የእንኳን ደስ አላችሁ በማለትም ባገኛችሁት ስኬት ሳትኩራሩ፣ ለበለጠ እንድትተጉ ሲሉ አስገንዝበዋል።   የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ በበኩላቸው በክልሉ መንግስት ሽልማትና እውቅና የተሰጠው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ስራን በጥራትና በብዛት መፈፀም የቻሉ አካላትን ለማበረታታት ነው ብለዋል። በተለይ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በሁሉም የልማት መስኮች፣ በፀጥታና በመልካም አስተዳደር፣ በገቢ አሰባሰብና በተለያዩ ኢኒሼቲቮች ህብረተሰቡን በተጨባጭ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። ዞኖች፣ ወረዳዎች፣ ከተሞችና ቀበሌዎች ካላቸው መዋቅራዊ አደረጃጀት አኳያ እርስ በእርሰ እንዲወዳደሩ ጥረት መደረጉንም ገልፀዋል። እውቅናና ሽልማቱ የተሻለ የሰሩትን ለማበረታታትና የአፈፃፀም ክፍተት ያለባቸው ደግሞ እንዲያስተካክሉ ማድረግን ያለመ ነው ብለዋል። በመሆኑም በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የገጠርና የከተማ ቀበሌዎችና ወረዳዎች፣ ዞኖች፣ ለከተሞችና የክልል ሴክተሮች እውቅናና ሽልማት መሰጠቱን አመልክተዋል። ይህም እውቅና በየደረጃው የህዝብን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ጠንካራ መዋቅር ለመገንባት መነሳሳትንና የውድድር መንፈስን ለማጎልበት ያስችላል ነው ያሉት።
ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ
Jul 15, 2025 241
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፦ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፤ በፑንትላንድ የሚንቀሳቀሰው የአይ ኤስ የሶማሊያ ክንፍ በተለያዩ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ለመስፋፋትና የሽብር ቡድኑን ሴሎች ለመመስረት የሚያደርገውን ጥረት በተመለከተ የመረጃ ስምሪትና ጥናት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ የአይ ኤስ የሶማሊያ ክንፍ በኢትዮጵያ የሽብር መረብ ለመዘርጋት የሚያደርገውን ሙከራ በተመለከተ ከጅምሩ በመረጃና በማስረጃ ተደግፎ ጥብቅ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን በመግለጫው ያስታወቀው አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ፤ የሥጋት ደረጃውን በተመለከተ በየጊዜው ባከናወነው ግምገማ ተጋላጭነትን የሚያስከትሉና ወደ ብሔራዊ ደኅንነት ሥጋት የሚያድጉ ተጨባጭ ግኝቶች መለየታቸውን ጠቁሟል፡፡ እንደ መግለጫው፤ የተከናወነውን ተጨባጭ መረጃና ማስረጃ የማጠናቀር ሂደት ተከትሎ የሽብር ቡድኑ በፑንትላንድ አሰልጥኖ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያሰማራቸው 82 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከፌዴራል ፖሊስና ከክልል የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ከቡድኑ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸውና ሁለንተናዊ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች መካተታቸውን በመግለጽ፤ በተለይ በዓለም-አቀፍ የሽብር ቡድኑ በመረጃ ክንፍ የተደራጁ እንዲሁም በፋይናንስና በሎጀስቲክ እገዛ ሲያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው በመግለጫው ተመላክቷል፡፡ የሽብር ቡድኑ የጥፋት ተልዕኮውን ለማስፋፋትና ምልመላ ለማከናወን የሃይማኖት ተቋማትንና ሃይማኖትን እንደ ሽፋን ይጠቀማል ያለው የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መግለጫ፤ የሕዝብን አንድነትና ተከባብሮ የመኖር እሴት የሚሸረሽሩ ብሎም ለአመጽና ሁከት የሚያነሳሱ አስተምህሮዎችን ለማስፋፋት ሙከራ ሲደረግ እንደነበር በተጨባጭ ማስረጃ መረጋገጡን አስታውቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ፣ አዳማ፣ ሃሮማያ፣ ሻሸመኔ፣ ባሌ፣ ጅማና ሻኪሶ ከተማ ዙሪያ፤ በአማራ ክልል ከሚሴ አካባቢ፤ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞንና ሃላባ ቁሊቶ ከተማ፤ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማና በሐረሪ ክልል በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፤ ግለሰቦቹን ለመያዝ በተደረገው ስምሪት በየአካባቢው የሚገኘው ኅብረተሰብ ከደኅንነትና ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ያሳየው ተሳትፎ በመልካም አርዓያነት የሚጠቀስ እንደነበር የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መግለጫ ጠቁሟል፡፡ በቁጥጥር ስር ያልዋሉ የሽብር ቡድኑ አባላት ላይ የሚደረገው ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያመለከተው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ኅብረተሰቡም በየአካባቢው ሰላምን የሚያደፈርሱና ስጋት ሊፈጥሩ የሚችሉ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት አንደ ሁልጊዜው ለሚመለከታቸው የደኅንነትና የጸጥታ አካላት ጥቆማ በማቅረብ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ማህበራዊ
ልዩነትን ከግጭት በራቀ መልኩ በውይይት የመፍታት ባህል ሊዳብር ይገባል -የሀይማኖት አባቶች
Jul 16, 2025 81
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ልዩነትን ከግጭት በራቀ መልኩ በውይይት የመፍታት ባህል ሊዳብር እንደሚገባ የሀይማኖት አባቶች አሳሰቡ። በኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት አስተባባሪነት የሀይማኖት አባቶች በትግራይ መቀሌ ያደረጉትን የሰላም ጥሪ በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የሀይማኖት አባቶቹን በመወከል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እንደገለፁት፣ የሀይማኖት አባቶቹ በቆይታቸው ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ እና አመራራቸው እንዲሁም ከክልሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል።   የሀይማኖት አባቶቹ ለባለድርሻ አካላቱ የሰላም ጥሪ ማቅረባቸውንም ጠቁመዋል። የሀይማኖት አባቶቹ፣ በትግራይ ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መነጋገራቸውን ጠቅሰው፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፍታት እንደሚገባ ማስገንዘባቸውንም አስረድተዋል። ባለድርሻ አካላቱ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንደሚፈቱም ተስፋቸውን ገልፀዋል። የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤም በጉዳዩ ዙሪያ ያለውን በጎ አበርክቶ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ሀጂ ኢብራሂም አመልክተው፣ ልዩነትን ከግጭት በራቀ አኳሃን በውይይት ብቻ የመፍታት ባህል በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች ሊዳብር እንደሚገባም አሳስበዋል።
ሆስፒታሉ ሕክምና ለማግኘት ርቀን ስንሄድ ሲደርስብን የነበረውን እንግልትና ወጪ አስቀርቶልናል-ተገልጋዮች
Jul 16, 2025 58
ቦንጋ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦በአካባቢያቸው የተገነባው ቆንዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሕክምና ለማግኘት ርቀው ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልትና ከፍተኛ ወጪ ማስቀረቱን ተገልጋዮች ገለጹ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው ቆንዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በቅርቡ ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። በወረዳው የቆንዳ ከተማ ነዋሪ ገዋተራሻ መሸሻ ከዚህ ቀደም በአቅራቢያቸው ሆስፒታል ባለመኖሩ ከፍ ያለ ሕክምና ለማግኘት ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀው ስለሚጓዙ ለወጪና ለእንግልት ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል። በቅርቡ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው ቆንዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ይህን ችግር በመፍታት በቅርበት የተሻለ የጤና አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ገልፀዋል። ቀደም ሲል በአካባቢያቸው የተሟላ የጤና አገልግሎት የሚያገኙበት ሁኔታ ባለመኖሩ በተለይ በእናቶችና ሕጻናት ላይ ጉዳት ይደርስ እንደነበር ያስታወሱት ሌላው የወረዳው ነዋሪ ወይዘሮ ነቢላ አባፎጊ፣ የሆስፒታሉ መመረቅ ለአካባቢው ነዋሪዎች ትልቅ እፎይታ መፍጠሩን ተናግረዋል።   ሆስፒታሉ ለአካባቢው ማህበረሰብ ድካምና ወጪን ከማስቀረት ባለፈ ፍትሃዊ የጤና ተጠቃሚነትን እንደሚያረጋግጥም ገልጸዋል። በሆስፒታሉ አዋላጅ ነርስ የሆኑት ሲስተር መሠረት መንገሻ በበኩላቸው፣ ከዚህ ቀደም በጤና ጣቢያ የተሟላ አገልግሎት ስላልነበር በተለይ ነፍሰጡር እናቶችን ወደ ቦንጋና ጅማ ከተማ ሆስፒታሎች በሪፈር ለመላክ ይገደዱ እንደነበረ አስታውሰዋል።   የተመረቀው ሆስፒታል አስፈላጊ ግብአቶች ተሟልቶለት በሙሉ አቅሙ አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ ያለው ጥረት የብዙዎችን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ እንግልትን ያስቀራል ብለዋል። በወረዳው ሆስፒታል ባለመኖሩ ህብረተሰቡ ተገቢውን የጤና አገልግሎት እያገኘ እንዳልነበር የገለጹት ደግሞ የገዋታ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዱ አባግዲ፣ "አሁን የተመረቀው ሆስፒታል ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን የጤና አገልግሎት በከፍተኛ ሁኔታ ያሻሽለዋል" ብለዋል።   በቀን ቢያንስ ሦስት እናቶች ወደ ቦንጋና ጅማ ሆስፒታል በሪፈር እንደሚላኩ አስታውሰው፣ ይህም ለከፍተኛ እንግልትና ወጪ ይዳርጋቸው እንደነበር አመልክተዋል። ለአገልግሎት የበቃው ሆስፒታል ለህብረተሰቡ አስፈላጊውን አገልግሎት እንዲሰጥ በወረዳው በኩል አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉም ተናግረዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም በበኩላቸው እንዳሉት፣ የጤና ተቋማትን የማስፋፋትና አገልግሎት አሰጣጣቸውን የማሻሻል ሥራ እየተሰራ ይገኛል።   ይህም የህብረተሰቡን የጤና ተጠቃሚነት እያሳደገው መሆኑን ገልፀው፣ የተመረቀው የቆንዳ ሆስፒታልም የእዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። ሆስፒታሉ በሙሉ አቅሙ ወደአገልግሎት እንዲገባ አስፈላጊ ግብዓቶች እንዲሟሉ ይደረጋል ያሉት ሃላፊው፣ የአካባቢው ማህበረሰብም ተቋሙን በባለቤትነት በመደገፍ የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በቅርቡ በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ የተገነባውን የቆንዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋቸው የሚታወስ ነው።  
የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ስኬታማ በሆነ መንገድ ተከናውኗል - የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)
Jul 16, 2025 66
  አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ስኬታማ በሆነ መንገድ መከናወኑን የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) አስታወቁ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያየ1 2ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወረቀትና በበይነ መረብ ተሰጥቷል። የትምህርት ሚኒስትሩ፥ የፈተናውን መጠናቀቅ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ፈተናው ስኬታማ በሆነ መንገድ ተካሂዷል። ፈተናው በስድስት ዙር የተሰጠ መሆኑን ያወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ቀደም ከተሰጡት ፈተናዎች በተሻለ መልኩ የተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት ከ29 ሺህ በላይ ተፈታኞች በበይነ መረብ መፈተናቸውን ገልጸው፥በ2017 ዓ.ም 134 ሺህ በበይነ መረብ መሰጠቱን ገልጸዋል። ፈተናው በ139 ፈተና ጣቢያዎች መሰጠቱን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በ40 ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መካሄዱን አንስተዋል። የዘንድሮው ፈተና የታለመለትን ዓላማ ያሳካ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ በዲጂታል የሚሰጠውን ፈተና ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በሚቀጥለው ዓመት በበይነ መረብ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ቁጥር ወደ 50 በመቶ ከፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዘንድሮ 23 ነጥብ 2 በመቶ በበይነ መረብ መውሰድ መቻላቸውን ተናግረዋል። በቀጣይም በትምህርት ቤቶች ኮምፒውተሮችን ተደራሽ የማድረግ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በአፋር ክልል በአራት የተለያዩ ቦታዎች አዲስ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ተከስቷል
Jul 16, 2025 78
ሰመራ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል በአራት የተለያዩ ቦታዎች አዲስ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ መከሰቱን የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። የእሳተ ጎመራ ፍንዳታ ክስተቱን ተከትሎ በተለይም በጉብኝት ላይ የነበሩ የውጭ ሀገራት ቱሪስቶችን ትኩረት መሳቡን ቢሮው አስታወቋል። በክልሉ ቱሪዝም ቢሮ የቱሪዝም ሃብት ማስተዋወቅና ገበያ ልማት ዳይሬክተር አቶ አብዱ አህመድ፤ ከትናንት ጀምሮ ከዋናው ኤርታሌ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በአራት የተለያዩ ቦታዎች አዲስ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ተከስቷል ብለዋል።   ክስተቱ በቱሪስቶችም ሆነ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አለማድረሱን ጠቅሰው፤ ሁኔታው በተለይም በጉብኝት ላይ ያሉ የውጭ ሀገራት ቱሪስቶችን ቀልብ በእጅጉ ስቧል ብለዋል። በአካባቢው የሚገኙ ቱሪስቶች በቅርበት ሆነው በአድናቆትና መገረም በትኩረት እየተከታተሉት መሆኑንም ገልጸዋል።   የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ከመሬት በታች የሚገኘው የማግማ ግፊት ሲጨምር ወይም የምድር ቅርፊት ስንጥቆችን በመፍጠር አዳዲስ መውጫ መንገዶችን ሲያገኝ የሚከሰት መሆኑን የዘርፉ ተመራማሪዎች ይናገራሉ።
ኢኮኖሚ
የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል
Jul 16, 2025 83
ድሬዳዋ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለፁ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬዳዋ ተካሂዷል። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ፤ በማጠቃለያ ንግግራቸው በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮችና መሰራት ስላለባቸው ቀጣይ አቅጣጫዎች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሀገርንና ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው በተለይም የኑሮ ውድነትን በማቃለል ረገድ በቀጣይ ብዙ ስራዎች ይጠበቃሉ ብለዋል። በዚህ ረገድ ጅምሮቹ ጥሩ መሆናቸውን አንስተው እንደየ ክልሎቹ ነባራዊ ሁኔታ ምርቶችን በመለየትና አቅርቦትና ምርታማነትን በማሳለጥ በቀጣይም ብዙ መስራት ይገባል ብለዋል። በምርት አቅርቦት ረገድ የክልሎች ትብብርና ጥብቅ ትስስር አስፈላጊ በመሆኑ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።   የቅዳሜ እና እሁድ ግብይቶችን ጨምሮ ለገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በየደረጃው ያሉ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት ተጨማሪ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው የኮንትሮባንድ ንግድንና የገበያ አሻጥሮችን በጥብቅ በመከታተል ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም በቅንጅት መስራት ይገባልም ብለዋል። የድሃ ተኮር ፕሮግራሞችን አጠናክሮ መቀጠል፣ የአመጋገብ ባህል እንዲሻሻል መጣርና የምርት አማራጮችን ማስፋትም እንዲሁ። ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር መልካም ጅምሮች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ አደም የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥልቀት በማየት በዘላቂነት መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም የብድር ሁኔታን የማመቻቸት፣ የስልጠና እድሎችን የማስፋትና የሰዎች የአስተሳሰብ በመለወጥ ረገድ እንዲሁም የስራ እና የመሸጫ ቦታዎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውሉ አመራሩ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከተረጅነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት ከቤተሰብ እቅድ ጀምሮ የድጋፍና ክትትል ስራን በማጠናከር ከሌማት ትሩፋትና ሌሎች የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ኢኒሸቲቮች ትግበራ ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዲፈጠር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል አቶ አደም። የሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠትና ዘላቂ መፍትሄ ለመሻትም የመጠባበቂያ ክምችትን ማሳደግና ጠንካራ የአሰራር ስርአት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል። ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በጥንቃቄ በመለየት ለፈጣን ምላሽ፣ በቂና የተሟላ ዝግጅት አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ከ6 ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎችን ወደ ስራ የሚያስገቡ የተለያዩ ክህሎት መር ስልጠናዎችን መስጠት ተችሏል-ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል
Jul 16, 2025 89
ድሬዳዋ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ በተጠናቀቀው በጀት ከ6 ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎችን ወደ ስራ የሚያስገቡ የተለያዩ ክህሎት መር ስልጠናዎችን መስጠት መቻሉን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ገለጹ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬዳዋ ተካሂዷል። በመድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ የብልፅግና ፓርቲ ዋና መስሪያ ቤት እና የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አመራሮች፣ ሚኒስትሮች እና የየክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ከተረጅነት የመውጣት ጥረት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን በመቀነስ ረገድና ሌሎችም ጉዳዮችን በመዳሰስ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና የተመዘገቡ ውጤቶችን በተመለከተ በመድረኩ በስፋት ውይይት ተደርጓል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፤ በተጠናቀቀው በጀት አመት የዜጎችን የስራ ፍላጎትና ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከፍተኛ ጥረት ተደርጎ ውጤትም ተመዝግቧል ብለዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎችን ወደ ስራ የሚያስገቡ የተለያዩ ክህሎት መር ስልጠናዎችን መስጠት መቻሉንም ሚኒስትሯ ተናግረዋል። በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ4.5 ሚሊዮን ለሚልቁ ዜጎች ክህሎት መር የስራ ዕድል በሀገር ውስጥና በውጭ የስራ ዕድል እንዲያገኙ መደረጉንም ጠቅሰው በሀገር ውስጥ የተፈጠረው የስራ ዕድል ከተያዘው ዕቅድ በላይ መሆኑንም ገልጸዋል። የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ(ዶ/ር)፤ በበኩላቸው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ የሀገሪቷን ዘርፈ ብዙ ልማትና እድገት ማሳለጥ መቻሉን አንስተዋል።   የገበያ ንረትን እና የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት ረገድም በስፋት መሰራቱንና ውጤት መምጣቱን ተናግረዋል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ፣ በከተማዋ የሚስተዋሉ ማህበራዊና የምጣኔ ሃብት ችግሮችን ለማቃለል በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል።   በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ31 ሺህ በላይ ዜጎች ባሉ ፀጋዎች ተጠቅመውና በተመቻቸላቸው መደላድሎች ታግዘው ከተረጂነት ወደ አምራችነት እንዲሸጋገሩ መደረጉን ጠቅሰው በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
በበጀት ዓመቱ ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው
Jul 16, 2025 92
ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ):- በአዲሱ በጀት ዓመት ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ወደ ውጭ ከተላከ ቡና ከ2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡ በተጀመረው አዲስ በጀት ዓመት ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ውጭ በመላክ ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡   ወደ ውጭ ለመላክ የታቀደው የቡና መጠን ከተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት የ150 ሺህ ቶን ጭማሪ እንዳለው የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ወደውጭ የሚላከው የቡና መጠን በየዓመቱ እያደገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዘርፉ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ አርሶ አደሩ ማሳውን እንዲያድስ፣ ያረጁ የቡና ተክሎችን እንዲጎነድል እንዲሁም ልማቱን በጥራትና በስፋት እንዲያከናውን እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ እንደሀገር የቡና ምርትና ምርታማነት የማሳደግ፣ ጥራትን የማስጠበቅና ግብይትን የማዘመን ሥራዎች ላይ በማተኮር በዘርፉ እየተመዘገቡ ያለውን ውጤቶችን የሚያስቀጥሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ የቡና ጥራትን ለማስጠበቅ አዲስ የኤክስቴንሽን ፓኬጅ ተቀርጾ ወደ ስራ መግባቱን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ባለስልጣኑ ከክልሎች ጋር በመቀናጀት የአርሶ አደሩን ግንዛቤ የሚያሳድጉ ስልጠናዎችን እየሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል። የሲዳማ ክልል ቡና ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ በበኩላቸው ከክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ38 ሺህ 500 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን ተናግረዋል፡፡   ከቀረበው ቡናም ከ90 ከመቶ በላይ የሚሆነው ደረጃ 1 እና 2 መሆኑን ጠቁመው በ2018 በጀት ዓመት ከ40 ሺህ 169 ቶን በላይ ቡና ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም የቡና ምርትና ምርታማነት የሚጨምሩ ፓኬጆችን የመተግበር፣ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በተደራጀ መንገድ የማዘጋጀትና በጥምር ደን የማምረት ሥራው እንደሚጠናከር ገልጸዋል፡፡ በክልሉ የቡና ቴክኖሎጂ መንደሮችን በክላስተር በማደራጀት 18 ሺህ ሄክታር መሬት መልማቱን ጠቁመው በአዲሱ በጀት ዓመትም ይህንን ተግባር የማስፋት ሥራ ይሰራል ብለዋል።  
በኦሮሚያ ክልል በቡና ልማት የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ይሰራል
Jul 16, 2025 84
አዳማ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ):-በኦሮሚያ ክልል በቡና ልማት የተገኘውን ውጤት በማስፋፋት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራ የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ አስታወቁ። በክልሉ በ2017 በጀት አመት የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና አፈፃፀም፣ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ መድረክ ዛሬ በአዳማ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ፣ ቡና ለሀገሪቱ የብልጽግና ጉዞ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግ በክልሉ የቡና ልማትን ለማስፋፋት ባለፉት ስድስት ዓመታት በተደረገው ርብርብ አመርቂ ውጤት ታይቷል ብለዋል። በተለይ መንግሥት የቡና ምርትና ምርታማነትን በመጨመርና ጥራቱን በማሻሻል በዓለም ገበያ ተወዳዳሪነቱን የበለጠ በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግሩን እውን ለማድረግ በልዩ ትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል። በዚህም መንግስት፣ አርሶ አደሮች፣ ቡና ላኪዎችና ባለድርሻ አካላት ባደረጉት የተቀናጀ ጥረት በምርታማነትና በገቢ የተሻለ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል። በዚህም ህይወቱን በቡና ልማት ላይ የመሰረተው አርሶ አደር ተስፋ ሰጪ ውጤት በማግኘቱ የልማት ተሳትፎውን ይበልጥ ለማጠናከር በዚህ ዓመት ርብርብ እንደሚደረግ አስታውቀዋል። በዚህ ረገድ ቡና ላኪዎች አርሶ አደሩ ከልፋቱ የተሻለ ተጠቃሚ እንዲሆን ድጋፋቸውን ከማጠናከር ባሻገር በቡና ልማት በስፋት እንዲሳተፉ ጠይቀው የክልሉ መንግስትም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስረድተዋል። በክልሉ በቡና ልማት ረገድ የተገኘውን ውጤት ዘላቂነቱን ለማስጠበቅ በየደረጃው የሚገኘው አመራር በልዩ ትኩረት እንዲሰራም አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) በበኩላቸው ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ እንደ ሀገር በቡና ልማት ከፍተኛ ውጤት እየታየ መጥቷል ብለዋል።   የቡና ልማትን ከማስፋፋት ባለፈ በኤክስፖርት ግኝትም ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ውጤት የተመዘገበው ከሁሉም ክልሎች እና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መሥራት በመቻሉ እንደሆነ አመላክተዋል። ቡና ለውጭ ገበያ የማቅረቡ ሥራ ለዘመናት በተወሰኑ ላኪዎች ቁጥጥር ስር የነበረበትን ሁኔታ በመቀየር አርሶ አደሩን ጨምሮ አዳዲስ ላኪዎችም እንዲካተቱ አሰራር ተዘርግቷል ብለዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ወደ ውጭ ከተላከው 469 ሺህ ቶን ቡና 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን አስታውሰው በ2018 በጀት ዓመትም 600 ሺህ ቶን ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት መታቀዱን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ፣ በክልሉ የቡና ምርታማነትና ጥራት ለማሳደግ የተለያዩ ኢኒሼቲቮች ተቀርፀው በተደረገው ርብርብ አመርቂ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል።   በክልሉ ባለፉት አምስት አመታት የቡና ልማትን ለማስፋፋት በተደረገው ርብርብ በየአመቱ የሚተከለውን የቡና ችግኝ ብዛት በ23 በመቶ ማሳደግ መቻሉን አስታውቀዋል። በዚህም የክልሉን አመታዊ የቡና ምርት ከ4 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 15 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ማሳደግ መቻሉን አመልክተዋል። ከዚህም ባለፈ በክልሉ ከ3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሔክታር በላይ መሬት ላይ ቡና እየለማ መሆኑን ጠቅሰው የቡና ልማት ምርታማነትን በሔክታር ከ6 ነጥብ 5 ኩንታል ወደ 9 ኩንታል ማሳደግ እንደታቻለም አውስተዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮጵያ የዲጂታል ውህደት ዕድገትን እያስመዘገበች ነው 
Jul 15, 2025 157
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 8/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዲጂታል ውህደት ዕድገትን እያስመዘገበች ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ። 25ኛው የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ የፋይናንስ ሚኒስትሮች ስብሰባ በኬኒያ ናይሮቢ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ የተሳተፉት ሚኒስትር ዴኤታው ኢትዮጵያ የዲጂታል ውህደት በመፍጠር በኩል ጠንካራ የዲጂታል ግስጋሴ ላይ መሆኗን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዲጅታል ግስጋሴ ከአፍሪካ ቀንድ የዲጂታል ፖሊሲ ማትሪክስ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ቀንድ ዲጅታል ውህደትን እውን ከማድረግ አንጻር ሀገራቱ ጥሩ አፈጻጸም እያስመዘገቡ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ኢትዮጵያ የተሻለ አፈፃፀም ካላቸው መካከል አንዷ መሆኗን ነው የገለጹት፡፡ ኢትዮጵያ ያደረገችው ሪፎርም የቴሌኮም ዘርፎችን ነፃ ማድረግ፣የግል መረጃ ጥበቃ እና የሳይበር ደህንነት ህጎችን ማውጣት፣የፋይበር መሠረተ ልማትን ማስፋፋት መቻሉን ገልጸዋል። እንዲሁም ከ19 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በዲጂታል መታወቂያ ስርዓት መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። አክለውም፥ ከ54 ሚሊዮን በላይ የቴሌብር ተጠቃሚዎች መኖራቸውን እና 4.6 ትሪሊዮን ብር የግብይት መጠን መፈጸሙ ኢትዮጵያ በፋይናንሺያል አካታችነት ያላትን ተነሳሽነት ያሳያል ብለዋል። የቀጣናውን የሀይል ትስስር አስፈላጊነት ገልጸው፥አጋር አካላት ለሚያደርጉት ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አመስግነዋል።
በሀገር ደረጃ የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ተደራሽ እየተደረጉ ነው - የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት
Jul 13, 2025 198
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በሀገር ደረጃ የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ጸጋ ገለጹ። ባለፉት የለውጥ አመታት 280 የሚሆኑ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ጸጋ ኢንስቲትዩቱ በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ጥናት የሚያደርግ ተቋም ነው ብለዋል። በዚህም 52 የትኩረት መስኮችን በመለየት በ14 ዲፓርትመንቶች 6 ማእከሎችን በማዘጋጀት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የምርምር ስራዎቹም በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን አመላክተዋል። ማስረጃን መሰረት ያደረጉ የጥናት ውጤቶችንም ለሚመለከታቸው ፖሊሲ አውጪዎች እና አስፈጻሚዎች ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት 280 የሚሆኑ ምርምሮች መደረጋቸውን ተናግረዋል። እነዚህ ምርምሮችም ነባር ፖሊሲዎችን የፈተሹ፣ አዳዲስ ፖሊሲዎችን ያመላከቱ እና ፋይዳ ምልከታ ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የጥናት መነሻዎቹ እንደ ሀገር የተቀመጡ እቅዶች እና የመንግስት አቅጣጫዎች መሆናቸውን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ፈጣን እደገት ያስመዘገቡ ሀገራት ትልልቅ የምርምር ተቋማት እንዳላቸው አንስተዋል። እንደ ሀገር የተቀመጡ ግቦች እና ህልሞች እውን እንዲሆኑ በጥናት መደገፍ እንደሚገባ በመግለጽ። ኢንስቲትዩቱ በዚህ ረገድ የተሰጠውን ተልእኮ በመውሰድ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ጥናቶችን በማጥናት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በተለዩ የትኩረት መስኮች ላይ ፖሊሲዎች ከመነደፋቸው በፊት የምርምር ስራዎች እንደሚሰሩ አንስተው፤ ተፈጻሚ ከሆኑ በኋላም ምን አይነት ውጤት አመጣ የሚለው እየተሰራበት መሆኑን ገልጸዋል። ለአንድ ሀገር እድገት ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶች አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ኢንስቲትዩቱም እንደ ሀገር የተቀመጡ ራእዮች እና ግቦች እውን እንዲሆኑ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶችን ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አመላክተዋል። በዚህ አመትም በኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ 35 ጥናቶች መጠናታቸውን ተናግረዋል።  
ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከ19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች ተመዝግበዋል
Jul 13, 2025 156
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እስካሁን ከ19 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች መመዝገባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ገለጹ። በኢትዮጵያ የነዋሪዎችን የመታወቅ መብት ለማረጋገጥ፣ በአገልግሎት ሰጭና ተቀባዮች መካከል መተማመን እንዲዳብር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና የተሳለጠ አሰራር ለመዘርጋት የዲጂታል መታወቂያ ገቢራዊ ተደርጓል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዘርፍ ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት በአዲስ አበባ እና በክልል የዲጂታል የመታወቂያ ምዝገባ ማከናወንና ከተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ፡፡ ይህንን ተከትሎ እስካሁን 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን ነዋሪዎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውንና ከ55 ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል ፡፡   በ2018 በጀት አመት የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን የበለጠ ለማሳደግ እቅድ መያዙንና ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡ በተለይ በክልሎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን ይበልጥ ለማስፋት ከተቋማት ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት አመት በክልሎች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መሰራቱን እና በዚህም ውጤት መገኘቱንም አስታውቀዋል።   ለዚህ ከከፍተኛ አመራሩ ጀምሮ ለስራው ትኩረት ሰጥቶ ህብረተሰቡ የዲጂታል መታወቂያ እንዲመዘገብ በማድረግ በኩል ትልቅ ተግባር ተከናውኗል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ትምህርት ማህበረሰቡ የፋይዳ ዲጂታል ትግበራ በትምህርት ቤቶች ውጤታማ እንዲሆን ያከናወነውን ተግባር በተሞክሮነት ወደ ክልሎች የማስፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለጻ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት የዲጂታል አገልግሎቱን ለማሳለጥና ጠንካራ የሆነ የማንነት አስተዳደር ስርዓት ለመፍጠር እያገዘ ይገኛል፡፡
በክረምት በተከታተልነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስልጠና የቀሰምነው ዕውቀት በትምህርት ቤት ውጤታማ እንድንሆን አግዞናል
Jul 12, 2025 164
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የታዳጊዎች የክረምት ስልጠና የቀሰሙት ዕውቀት በትምህርት ቤት ውጤታማ እንዲሆኑ እንዳገዛቸው ቀደም ሲል የሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤ አይ) ስልጠና የተከታተሉ ታዳጊዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በተለያዩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች አራተኛውን የታዳጊዎች የክረምት ስልጠና በሳይንስ ሙዚየም አስጀምሯል። ስልጠናውን ተከታትለው የጨረሱ ታዳጊዎች ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ ቀደም ሲል የወሰዱት ስልጠና ህልማቸውን እውን ለማድረግ በሚሰሩት ስራ በብዙ መንገድ ደግፏቸዋል። በትምህርት ማዘመን የሚያስችል ፕሮጀክት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ወጣት ሰለሞን መብሬ የ2014 የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስልጠና ወስዶ አጠናቋል። እንደወጣት ሰለሞን ገለጻ፤ አሰልጣኞቹ በዘርፉ ያላቸው እውቀት ከፍተኛ በመሆኑ ፈጠራን ለመውደድና ለማሰብ አስችሏቸዋል። በዚህም የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ወደ ጥቅም መቀየር የሚያስችል አቅም ማዳበራቸውን ጠቁሞ፤ በተለይ በቡድን የመስራት መንፈስ እንዲላበሱ እንደረዳቸው ተናግሯል። የ12ኛ ክፍል ተማሪ ዲቦራ ወንድወሰን የ2015 የሰው ሰራሽ አስተውሎት የክረምት ስልጠና ተመራቂ ነች። በተከታተለቸው ስልጠና በአጭር ጊዜ ውስጥ አዳዲስ ነገሮች ለመገንዘብ መቻልዋን ተናግራለች። እንዲሁም በቡድን የመስራት ችሎታና ችግሮችን የመፍታት አቅም ለማዳበር እንደረዳትም ነው የገለፀችው። አስተያየት ሰጪዎቹ ስልጠናው የሀገር ብሎም የማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚያስችሉ መርሃ ግብሮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተናግረዋል። በዚህም የአራተኛውን ዙር የሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤአይ) የክረምት ስልጠና የሚወስዱ ታዳጊ ተማሪዎች ያገኙትን እድል በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል። በሌላ በኩል ዘንድሮ ወደ ስልጠናው የሚገቡ ሰልጣኞች በበኩላቸው፤ በስልጠናው የተሻለ እውቀትና ችሎታ አዳብረው ለመውጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ተማሪ ቅዱስ ሙሴ የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት(ኤአይ) መማር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን በማመን ወደ ስልጠናው መምጣቱን ተናግሯል። ታዳጊዎች እንደዚህ ዓይነት ስልጠናዎች መሳተፋቸው ትልቅ ህልም እንዲያልሙ ና ህልማቸውን በተጨባጭ በመተርጎም ከራሳቸው አልፈው ለሀገር እንዲተርፉ ይረዳል ብሏል። የስምንተኛ ክፍል ተማሪ ኑሃሚን ጥበቡ እንደምትናገረው፤ አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ ስራዎችን ቀለል ባለ መልኩ ለማከናወን የሚረዳ በመሆኑ ሥልጠናውን ለመከታተል ፍላጎት አሳድሮባታል። በዚህም ዘንድሮ በሚሰጠው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የክረምት ስልጠና በምታገኘው እውቀት ፓይለት የመሆን ህልሟን እውን ለማድረግ እንደሚያግዛት ታምናለች።
ስፖርት
ኢትዮጵያ በአፍሪካ የታዳጊ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የመክፈቻ ቀን አራት ሜዳልያዎችን አግኝታለች
Jul 17, 2025 41
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017 (ኢዜአ)፦ ሶስተኛው የአፍሪካ ከ20 እና 18 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ማምሻውን በናይጄሪያ አቡካታ ተጀምሯል። በመክፈቻው የኢትዮጵያ አትሌቶች የተሳተፉባቸው አምስት የፍጻሜ ውድድሮች ተካሄደዋል። በ1500 ሜትር ሴት ከ18 ዓመት በታች ፍጻሜ ኤልሳቤጥ አማረ የብር፣ ደስታ ታደሰ የነሐስ ሜዳልያ አግኝተዋል። አትሌት ትርሃስ ገብረህይወት በ3000 ሜትር ሴቶች ከ20 ዓመት በታች የፍጻሜ ውድድር የብር ሜዳልያ አግኝታለች። እንዲሁም በ1500 ሜትር ወንድ ከ18 ዓመት በታች ሳሙኤል ገብረሃዋርያ የነሃስ ሜዳልያ ለሀገሩ ማስገኘቱን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በስሉስ ዝላይ ሴት ከ20 ዓመት በታች ፍፃሜ ኛቾክ ቾል፣ አትሌት ንብረት ክንዴ በ10000 ሜትር ወንድ ከ20 ዓመት በታች ፍፃሜ ደረጃ ውስጥ አልገቡም። በአጠቃላይ በሻምፒዮናው መክፈቻ ኢትዮጵያ ሁለት ብር፣ ሁለት ነሐስ በድምሩ አራት ሜዳልያዎች አግኝታለች። ኢትዮጵያ በውድድሩ ላይ 30 ወንድ እና 27 ሴቶች በድምሩ 57 አትሌቶችን ታሳትፋለች። ሶስተኛው የአፍሪካ ከ20 እና 18 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
በአፍሪካ የታዳጊ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ አትሌቶች የሚሳተፉባቸው አምስት የፍጻሜ ውድድሮች ይካሄዳሉ 
Jul 16, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ):- በናይጄሪያ አቡካታ የሚካሄደው ሶስተኛው የአፍሪካ ከ18 ዓመት እና ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀመራል። በሻምፒዮናው ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ43 ሀገራት የተወጣጡ 937 አትሌቶች ይሳተፋሉ። በውድድሩ ላይ ኢትዮጵያ 30 ወንድ እና 27 ሴቶች በድምሩ 57 አትሌቶችን ታሳትፋለች። አጠቃላይ 69 የአትሌቲክስ ልዑክ ወደ ስፍራው አምርቷል። በሻምፒዮናው መክፈቻ ቀን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው አምስት የፍጻሜ ውድድሮች ይካሄዳሉ። በ1500 ሜትር ሴት ከ18 ዓመት በታች ፍፃሜ ኤልሳቤጥ አማረ፣ ደስታ ታደሰ እና ቦንቱ ዳንኤል ይሳተፋሉ። ምሽት 1 ሰዓት ከ35 ላይ ስሉስ ዝላይ ሴት ከ20 ዓመት በታች ፍፃሜ ኛቾክ ቾል ትወዳደራለች። አትሌት ሳሙኤል ገብረሃዋርያ እና አትሌት አብርሃም ገብረእግዚአብሔር ምሽት 1 ሰዓት ከ40 ላይ በሚካሄደው 1500 ሜትር ወንድ ከ18 ዓመት በታች ፍፃሜ ላይ ይሳተፋሉ። ምሽት 3 ሰዓት ከ10 ላይ በ3000 ሜትር ሴት ከ20 ዓመት በታች ፍፃሜ ቤተልሄም ጥላሁን ትርሐስ ገብረህይወት እና ውድነሽ አለሙ የሚወዳደሩ ይሆናል። አትሌት ንብረት ክንዴ ምሽት 3 ሰዓት ከ25 በ10000 ሜትር ወንድ ከ20 ዓመት በታች ፍፃሜ ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ ይወዳደራል። ከፍጻሜ ውድድሮቹ በተጨማሪ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው የማጣሪያ ውድድሮች ይካሄዳሉ። በሻምፒዮናው ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች የተመረጡት በድሬዳዋ ከተማ በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም በተካሄደው 13ኛው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና እና 4ኛው የኢትዮጵያ ከ18 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ባስመዘገቡት ውጤት መሆኑን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። ሶስተኛው የአፍሪካ ከ18 ዓመት እና ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
የሴቶች አውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሃ ግብር ዛሬ ይጀመራል 
Jul 16, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017 (ኢዜአ):- በ14ኛው የሴቶች የአውሮፓ ዋንጫ የመጀመሪያው የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ በአየርላንድ እና ጣልያን መካከል ዛሬ ይደረጋል። የሁለቱ ሀገራት ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት በጄኔቭ ስታዲየም ይካሄዳል። የሁለት ጊዜ የአውሮፓ ዋንጫ አሸናፊዋ ኖርዌይ በምድብ አንድ ያደረገቻቸውን ሶስት ጨዋታዎች በማሸነፍ በዘጠኝ ነጥብ የምድቧ መሪ ሆና አልፋለች። ተጋጣሚዋ ጣልያን በምድብ ሁለት በአራት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች። ሁለቱ ቡድኖች እስከ አሁን በውድድር እና ወዳጅነት ጨዋታዎች 12 ጊዜ እርስ በእርስ ተገናኝተዋል። ኖርዌይ 7 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ስትይዝ ጣልያን 2 ጊዜ ድል ቀንቷታል። ሁለት ጊዜ አቻ ወጥተዋል። ኖርዌይ በጨዋታዎቹ 21 ግቦችን ስታስቆጥር ጣልያን 14 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ሁለቱ ቡድኖች በተገናኙባቸው ጨዋታዎች በአንድ ጨዋታ በአማካይ ከሁለት ግቦች በላይ ይቆጠራል። ሀገራቱ እ.አ.አ በ2024 ለ14ኛው የሴቶች አውሮፓ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ባደረጓቸው ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል (1-1 እና 0-0)። ኖርዌይ እ.አ.አ 1987 እና 1993 የሴቶች አውሮፓ ዋንጫን አሸንፋለች። በ1987 ዋንጫውን ያነሳቸው አዘጋጇ ሀገር ጣልያንን በማሸነፍ ነበር። ጣልያን እ.አ.አ 1993 እና 1997 ለፍጻሜ ደርሳ በቅደም ተከተል በኖርዌይ እና ጀርመን ተሸንፋ ዋንጫውን አጥታለች። ኖርዌይ የሩብ ፍጻሜን ጨዋታ የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት አግኝታለች። የጨዋታው አሸናፊ በግማሽ ፍጻሜው ከእንግሊዝ እና ስዊድን አሸናፊ ጋር ይገናኛል። በስዊዘርላንድ እየተካሄደ የሚገኘው 14ኛው የሴቶች የአውሮፓ ዋንጫ ዛሬ 15ኛ ቀኑን ይዟል።
አካባቢ ጥበቃ
አረንጓዴ አሻራ ምቹ፣ ውብና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ሀገርን ለመጪው ትውልድ የማስተላለፍ ተግባር ነው
Jul 16, 2025 81
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እያካሄደችው የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ምቹ፣ ውብና ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ የማይበገር ሀገርን ለመጪው ትውልድ የማስተላለፍ ተግባር መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል። በዚህም የተለያዩ ተቋማትና ህብረተሰብ ክፍሎች በሁሉም የአገሪቷ አካባቢዎች አሻራቸውን በማሳረፍ ላይ ይገኛሉ። ዛሬ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አመራር አባላትና ሰራተኞች፣ ከፌዴራል ስፖርት ማህበራት፣ ከኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፣ ከሸገር ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት አመራር አባላትና ሰራተኞች ጋር በመተባበር በገላን ስታዲዬም የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማህዲ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምቹና ውብ አካባቢን በመፍጠር ለመጪው ትውልድ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ የማይበገር ሀገርን የማስረከብ ተግባር ነው። ይህንን እውን ለማድረግ ወጣቱ እያደረገ ያለውን አበርክቶና ተነሳሽነት አድንቀዋል፡፡   ባለፉት ሰባት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ የተሰሩ ስራዎች በህብረተሰቡ ዘንድ ባህል እየሆኑ መምጣታቸውን የተናገሩት ደግሞ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሀመድ ናቸው።   ይህም ዛሬ በተግባር የታየበት መሆኑን ገልጸው፣ በቀጣይም የተተከሉ ችግኞች ጸድቀው የታለመው አላማ እንዲሳካ እንሰራለን ብለዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በበኩላቸው እንደገለጹት ፌዴሬሽኑ ለአረንጓዴ አሻራ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።   የሸገር ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ናስር ሁሴን፤ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ ችግኞችን መትከል ስፖርተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ባህል እንዲያደርጉና እንዲንከባከቡ ለማስቻል ነው ብለዋል።   ከተሳታፊዎች መካከል የአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ከፍለ ከተማ ወረዳ 13 ነዋሪ ወጣት በድሉ በቀለ እና በሸገር ከተማ አስተዳደር ቡራዩ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ወጣት ቡሳሞ ሞንደ እንዳሉት በየዓመቱ በሚካሄዱ የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብሮች ላይ በመሳተፍ አሻራቸውን እያኖሩ ነው።     ችግኞችን መትከልና እስከ ጽድቀታቸው ድረስ መንከባከብ ከሁሉም ሰው የሚጠበቅ ተግባር መሆኑንም ተናግረዋል።
በአፋር ክልል አፍዴራ ወረዳ በጣለው ከባድ ዝናብ ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ ድጋፍ እየተደረገ ነው
Jul 16, 2025 61
አፋር፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል አፍዴራ ወረዳ በጣለው ከባድ ዝናብ ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስራ አመራር ኮሚሸን አስታወቀ፡፡ በክልሉ በትናንትናው እለት ነፋስ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱም ታውቋል። የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሎጀስቲክስ ኦፕሬሽን ምክትል ዳይሬክተር አሊ መሀመድ፤ ክስተቱን በማስመልከት ለኢዜአ መረጃ ሰጥተዋል። በክልሉ አፍዴራ ወረዳ በትናንትናው እለት ነፋስ ቀላቅሎ የጣለው ከባድ ዝናብ በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱንና ብዙዎችን ማፈናቀሉንም ተናግረዋል።   በአደጋው ምክንያት በ32 ሰዎች ላይ ከባድ እንዲሁም በ22 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት ማድረሱን ጠቅሰው፤ ተጎጂዎች የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ገልጸዋል። በአደጋው ከ2 ሺህ 500 በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን አንስተው ፤ አምስት የጨው ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችም ጉዳት እንደደረሰባቸው ጠቅሰዋል። ክስተቱን ተከትሎ ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የምግብ፣ አልባሳትና የፍራሽ ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰው፤ ቀጣይነት ያለው እገዛና ድጋፍ የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል። ለአደጋው አስቸኳይ ምላሽ የሚሰጥ ከተለያዩ አካላት የተዋቀረ ግብረ ሃይል መቋቋሙን ተናግረው ፤ ቅንጅታዊ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከወረዳው አስተዳደር፣ ከጸጥታ ሃይል፣ በየደረጃው ካለው አመራርና አጠቃላይ ህብረተሰቡ ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።  
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሌሎች አገራት ምሳሌ የሚሆን ተግባር እያከናወነች ነው - የተለያዩ አገራት ወታደራዊ አታሼዎች
Jul 16, 2025 76
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሌሎች አገራት ምሳሌ የሚሆን ተግባር እያከናወነች ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ አገራት ወታደራዊ አታሼዎች ገለጹ። የመከላከያ ሠራዊት የዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በመከላከያ ሚኒስቴር ጠቅላይ መምሪያ ዋና ግቢ ተካሂዷል። በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ ጄኔራል መኮንኖችና የተለያዩ አገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ወታደራዊ አታሼዎች መካከል በኢትዮጵያ የማላዊ ወታደራዊ አታሼ ብርጋዴር ጄኔራል ክሪስፒን ሮበርት ፒሪ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ ትምህርት የሚቀሰምበት ስራ እያከናወነች ትገኛለች።   ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና ለመቀነስ እያከናወነች ያለችውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አፍሪካ ብቻ ሳይሆን መላው ዓለም አርአያ ማድረግ እንደሚገባው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የጣሊያን ወታደራዊ አታሼ ኮሎኔል ማርኮ ፖዲዲ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ አሻራ ከብክለት የፀዳ ዓለምን ለትውልድ ለማስተላለፍ ወሳኝ ነው።   በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ለዓለም ምሳሌ ሊሆን የሚችል ተግባር እያከናወነች እንዳለ መመልከታቸውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ ለዓለም አገራት ምሳሌ ሊሆን የሚችል ተግባር እያከናወነች ነው ያሉት በአፍሪካ ህብረት እና በኢትዮጵያ የሞዛምቢክ ወታደራዊ አታሼ ኮሎኔል ፈርናንዶ ማከንዚ ጂሞ ናቸው።   በቀጣይ ኢትዮጵያን ምሳሌ በማድረግ በርካታ አገራት በዚህ መርሃግብር እንደሚሳተፉ ኮሎኔሉ ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ሰባት ነጥብ አምስት ቢሊየን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።  
ሰራዊቱ አረንጓዴ ዐሻራን ባህል የማድረግ ሥራውን አጠናክሮ ይቀጥላል - ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
Jul 16, 2025 112
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦ ሰራዊቱ በመኖሪያ ካምፕ እና በግዳጅ ቀጣናው አረንጓዴ ዐሻራን ባህል የማድረግ ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል።   የመከላከያ ሰራዊት የዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በመከላከያ ሚኒስቴር ጠቅላይ መምሪያ ዋና ግቢ ተካሂዷል። በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ ጄኔራል መኮንኖችና የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ ሰራዊቱ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ከፍተኛ ተሳትፎ አድርጓል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር እንደሀገር ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የደን ሽፋንን በማሳደግ፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥና የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል። የመከላከያ ሰራዊቱም የበኩሉን ሚና በመወጣት ዐሻራውን እያኖረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።   የዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ከዛሬ ጀምሮ ሰራዊቱ በያለበት የግዳጅ ቀጣና እና በመኖሪያ ካምፖች ጭምር ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ዐሻራን ባህል የማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ቶማስ ቱት በበኩላቸው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከተሰጠው ግዳጅ ጎን ለጎን በአካባቢ ጥበቃ ላይ በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል ብለዋል። በዘንድሮ አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በመከላከያ ሰራዊት ከ18 ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል እና ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች እንደሚተከሉም አስታውቀዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 1057
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ።   በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1376
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል።   የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 1044
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል።   ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1672
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
የህንድ የፈጠራ ማዕከል - ባንጋሎሩ
Jul 2, 2025 559
ቤተልሄም ባህሩ(ኢዜአ) የዴልሂና አግራ ቆይታችንን ጨርሰን ወደ ቀጣይ መዳረሻችን ባንጋሎሩ ከተማ ልንጓዝ ስንሰናዳ አብዛኛው የጋዜጠኛ ልዑክ ያሳሰበው እንደሰም የምታቀልጠውን የአግራ ፀሀይና ሙቀት በባንጋሎሩም ታገኘን ይሆን? የሚለው ነበር። ሆኖም ከዴልሂ ኢንድራ ጋንዲ አየር ማረፊያ ተነስተን ለሶስት ሰዓት ከተቃረበ በረራ በኋላ ያገኘናት ባንጋሎሩ የተለየች ሆነን አገኘናት። ባንጋሎሩ ቀዝቀዝ ባለ አየር ነበር እንግዶቿን የተቀበለችን። በዕለቱ ከክፍሎቻችን ወጥተን በጋራ ወደአየር ማረፊያ የሚወስደንን ትራንስፖርት ስንጠባበቅ ከጋዜጠኛ ቡድኑ ስድስት አባላት ከአጠገባችን እንዳልነበሩ አስተዋልን። የት ጋር እንደተነጣጠልን አላስታውስም። በዚህ ምክንያት ግን የእለቱ ጉዟችን ተሰርዞ ከተማዋን ለማየት ስንዘዋወር የማውቀው ዓይነት እንጂ የተለየ ሙቀት አላስተናገድኩም። የ13 ወር ፀጋ በመባል የምትታወቀው አገሬ ኢትዮጵያ ከዳሎል እስከ ራስ ዳሽን ባላት የመልከዓ ምድር አቀማመጥና ልዩ ልዩ የአየር ጠባይ ሙቀቱንም፣ ቅዝቃዜውንም ማወቃችን እንደዚህ ለአለ አጋጣሚ መልካም ስሜት ይፈጥራል። በተወሰነ ደረጃ በህንድ ያጋጠመኝ የአየር ባህሪ ከአገሬ ጋር ቢመሳሰልብኝ የፈጣሪንና የተፈጥሮን ስራ አጃኢብ ብዬ እንዳልፍ አድርጎኛል። ባንጋሎሩ ከተማ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የህንድ ሲልከን ቫሊ በመባል ትታወቃለች። ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎችም ከመገለጫዎቿ መካከል ናቸው። የጠፈር ጠበብቶቹ - ባንጋሎሩ ደርሰን በመጀመሪያ ያየነው ዓለም በስፔስ ሳይንስ እየሰራች ያለችውና እያስመዘገበችው የምትገኘው ውጤት ማሳያ የሆነውን የህንድ ስፔስ ምርምር ድርጅትን ነው። ተቋሙ የህንድ መንግስት የስፔስ ዲፓርትመንት አካል ሲሆን፤ ዶክተር ቪክራም ሳራብሃይ በተሰኙ ባለራዕይ በ1962 የተወጠነና አሁን ላይ በዘርፉ ተገዳዳሪ መሆን የቻለ ነው። የተቋሙ ዓላማ የስፔስ ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመተግበር ለተለያዩ አገራዊ ጥቅሞች ማዋል መሆኑን ተከትሎ የሳተላይት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማምረት ስራን ጨምሮ ከአገሩ አልፎ ለሌሎች አገራትም በዘርፉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። የተደረገልን ገለፃ አብዛኛውን ጋዜጠኛ ያስደመመ ነበር ከገለፃ በኋላ በጋዜጠኞች የተነሳው ሃሳብም ህንድ በስፔስ ዘርፍ ያላት ልምድና ያከናወነችው ተግባር በቀጣይም ልትሰራ የወጠነቻቸው ሃሳቦች የአገሪቱን መዳረሻ የተለሙ በአገራቸው እንዲተገበር የሚናፍቁት መሆኑን ነው። ተቋሙ በዘርፉ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን የሚያጠናክር መሆኑን ከተደረገልን ገለፃ ተገንዝበናል።   በሳይንስ፣ ኢንጂነሪንግና አስተዳደር ምሁራንን በማስተማር እያበረከተ ያለው የህንድ የሳይንስ ኢንስቲትዩት በባንጋሎሩ ከጎበኘናቸው መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የተውጣጡ ተማሪዎችን የሚያስተምርና ከተቋማት ጋርም በዘርፉ የሚሰራ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ከጅማ፣ በተግባር ለመቀየር ሲታትሩ የስታርት አፖችን የምርት ውጤቶቻቸውን ሲፈትሹና ሲሞክሩ ተመልክቻለሁ። በኢትዮጵያም አሁን ላይ ለስታርት አፖች በተሰጠው ትኩረትና በተፈጠረው ምቹ ስነ ምህዳር የፈጠራ ውጤቶች እያደጉና እየተበራከቱ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። እንደ አዳማና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት የተማሪዎችን ፈጠራ ወደ ውጤት ለመቀየር እየተጉ መሆኑና የስታርት አፕ ኤግዚቢሽንና የሰመር ቡት ካምፖች ፈጠራን ምን ያህል እያበራከቱ መሆናቸው በጉብኝቱ ወቅት ወደ አዕምሮዬ የመጣ የአገሬው ህዝብ በውጤት የታጀበ ጥረት ነው።   ከአራት አስርት ዓመታት በላይ በባዩቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘው ባዮኮንም ከባላንጎሩ የጉብኝት መዳረሻችን መካከል የሆነና አስፈላጊ መድሀኒቶችን የሚያመርትና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይም እየሰራ ያለ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተጠቃሚ ናቸው። ከ120 በላይ በሆኑ አገራት ለስኳርና ካንሰር ህመም የሚያገለገሉ መድሀኒቶችን በማምረትና በማሰራጨት ለህሙማን ፈውስና ለጤናው ዘርፍ ስርዓት አስተዋፅኦ እያበረከተም ይገኛል። የተቋሙ ላቦራቶሪና ዘመኑን የዋጀና ደረጃውን የጠበቀ ማምረቻ ፋብሪካን መጎብኘቴ አለም በፋርማሲዩቲካልስ ዘርፍ ያለችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። የባንጋሎሩ ቤተመንግስት - ይህን ቤተ መንግስት ማስቃኘቴን ከመጀመሬ በፊት በስፍራው ካስገረመኝ ነገር ላወጋችሁ ወደድኩ። ቤተ መንግስቱን ለመጎብኘት ያቀናነው በእለተ ሰኞ ነበር። ሆኖም ምድረ ግቢውን ቃኝተን ስለህንፃው ሰምተን ከመመለስ ውጪ ወደ ውስጥ አልዘለቅንም። ለምን? ለሚለው ምላሹ በዚህ ስፍራ "ሰኞ የእረፍት ቀን ናት" ነው። እንዴት ካላችሁ ቤተ መንግስቱ ቅዳሜና እሁድ በበርካታ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑን ተከትሎ በስፍራው ለሚሰሩ ሰራተኞች የእረፍት ቀናቸው ሰኞ በመሆኑ ነው። የቤተ መንግስቱ ምድረ ግቢ ሰፊና ልምላሜ የተላበሰ ሲሆን፤ የሚያምርና ለዓይን የሚስብ ኪነ ህንፃ ያለው ነው። አሰራሩና ውጥኑም እንደሚከተለው ነው። በዎዲየር ስርወ መንግስት ንጉስ ቻማራጃ ዋዲያር ወደ እንግሊዝ ባደረጉት ጉዞ በለንደን ዊንሶር ግንብ ይደነቃል። ተደንቆም አልቀረ የባንጋሎሩ ቤተ መንግስትን በተመሳሳይ ሁኔታ ይገነባል። ይህ ቤተ መንግስት በተወሰነ መልኩ የመካከለኛው ዘመን የኖርማንሲና የእንግሊዝ ግንቦችን ይመስላል።   ቪድሃና ሶውዳ የካራንታካ ህግ አውጪ አካል መናገሻ በጉብኝታችን ያየነው ሌላው መዳረሻ ስፍራችን ነው። የህግ አውጪና የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የያዘው ይህ ህንፃ ህንድ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ በራሷ መሀንዲስ የሰራችው የመጀመሪያው ህንፃ መሆኑ ተገልፆልናል። የህንፃ ግንባታ ጥበብ ማሳያ፣ የፖለቲካ መናገሻ እንዲሁም የባህል ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል።   እንደአጠቃላይ በቆይታዬ የተመለከትኩት የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ማበረታቻ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራ ኢትዮጵያ እያከናወነች ካለው የኮሪደር ልማትና ስታርት አፕን የማበረታታት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ምቹነት ስራዎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ነው። በህንድና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ዘመናትን የተሻገረ፤ ለሁለት ሺህ ዓመታት የዘለቀ መሆኑን የታሪክ መዛግብት ያሳያል። የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት በአክሱም ስርወ መንግስት ኢትዮጵያና ህንድ በአዱሊስ ወደብ በኩል የንግድ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያ ቅመማ ቅመምና ሐርን ከህንድ ትገበይ ነበር። ህንድ ደግሞ ወርቅና የዝሆን ጥርስን ከኢትዮጵያ ትሸምት ነበር። ህንድ ከንግድ ልውውጥ ባሻገር በኢትዮጵያ ኪነ ህንፃ ግንባታ ላይ አሻራዋን አኑራለች። በኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍም ትልቅ አበርክቶ ያላት አገር ናት። ህንድ ነፃነቷን ካገኘችበት እኤአ 1948 አንስቶ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት ኢትዮጵያና ህንድ ሌላው የሚያመሳስላቸው ነገር ሆኖ ያገኘሁት የአምራች ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያከናወኑ ያሉት ንቅናቄ ነው። ህንድ እ.አ.አ ከ2014 ጀምሮ የአምራች ዘርፉን ለማበረታታት "ሜድ ኢን ኢንዲያ" በሚል ለአስር ዓመት የተገበረችውና በርካታ ለውጥ የተመዘገበበት ንቅናቄ በኢትዮጵያ ከ2014ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ካለውና የሃገር በቀል ምርቶች እና አምራቾችን ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪያል ማህበረሰብ ግንባታን ማሳደግ ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢ መፍጠር እና የጥናት እና ምርምር ችግር ፈቺነትን ማሳደግን ዓላማ ካደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጋር የተመሳሰለ ነው። ንቅናቄ በኢትዮጵያ መተግበሩ ዓመታዊ የዘርፍ ዕድገት፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና ገቢ ምርት በመተካት በኩል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑም ይታወቃል። በህንድ ተዘዋውሬ በተመለከትካቸው ከተማዎች ባሉ ጎዳናዎች ከታዘብኩት ነገር ሰዎች ከሱቅ ለሚገበያዩት ነገር ሳይቀር በዲጂታል መንገድ ክፍያ መፈፀማቸውን ነው። በባጃጅና በሞተር የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘትም ጭምር ሞባይሉን በመጠቀም “ይህ ቦታ የት ነው?” ሳይል ያሻዎት ስፍራ መድረስም ሌላው ትዝብቴ ነው። ይህ ነገር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትኩረት አግኝተው እየተሰራባቸው ካሉት የዲጂታል ክፍያና ዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ መርሃ ግብር ጋር የሚመሳሰል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በቆይታችን ልክ እንደአትሌቶቻችን ሁሉ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርጎ የሚያስነሳውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝናና ክብር ለማስተዋል ችያለሁ። ፀጉረ ልውጥ መሆናችንን የተገነዘቡ በገበያ ማዕከላት የሚያገኙን እንዲሁም በምንጎበኛቸው ተቋማት የምንተዋወቃቸው ህንዳውያን "ከየት ናችሁ?" ብለው ሲጠይቁ፤ ለእኔና አንድ ከሌላ መገናኛ ብዙሃን የሄድን "ከኢትዮጵያዊ" ስንል የሚከተልልን ምላሽ "አሃ የኢትዮጵያ አየር መንገድ" የሚል ነው። ይህም አየር መንገዱ ስሙ ከኢትዮጵያ ተሰናስሎ የሚጠራ የአገሪቷ መታወቂያ ተቋም መሆኑን ያስገነዘበኝ ነው። ከህንዳውያን ጋር ብቻ ሳይሆን አብረን ከተጓዝን ጋዜጠኞች አንዱ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእናንተ የብቻ ሳይሆን እኛንም እንደራሳችን ሆኖ እያገለገለን ያለ የጋራ አየር መንገዳችን ነው" ሲል ነው የገለፀው። ይሄ ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገር ኩራት ብቻ ሳይሆን መለያ ምልክትም ጭምር መሆኑን የተረዳሁበት አጋጣሚ ነው። በቀናት ቆይታዬ በእንግዳ አክባሪነታቸውና በለገሱን ፍቅርና እንክብካቤ ከአገሬ የራቅኩ ያህል ሳይሰማኝ ብቸኝነትን ሳላስተናግድ እንደውም እየናፈኳቸው እንድመለስ ላደረጉኝ ህንዳውያን በከበረ ሰላምታ ላመሰግን እወዳለሁ።
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 512
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል።   ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል።   የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው።   የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው።   ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።    
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 1051
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች።   የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች።   ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ።   ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።      
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 1171
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 3505
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 2878
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 3068
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 4182
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2800
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2435
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3893
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48733
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 44102
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 28143
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25498
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 23725
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 21848
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 21712
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 21341
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48733
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 44102
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 28143
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25498
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ከሮም እስከ አዲስ አበባ 
Jul 11, 2025 300
ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ይካሔዳል። የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ኢንቨስትመንት እና ፋይናንስ፣ የምግብ ስርዓት ሽግግር ሁለንተናዊነትና የተገቡ ቃሎችን ከመፈጸም አንጻር ያለውን የተጠያቂነት ስርዓት ማጠናከር ጉባኤው ትኩረት ያሚያደርግባቸው ሀሳቦች ናቸው። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተምግብ ጉባኤ በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በጣልያን ሮም የተካሄደው የመጀመሪያ የተመድ ስርዓት ምግብ ላይ የተገቡ ቃሎች ትግበራ ሂደትን መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ነው። በመጀመሪያው ጉባኤ ላይ የ182 ሀገራት ተወካዮች፣ 21 የሀገራት መሪዎች እና 126 ሚኒስትሮችን ጨምሮ 3 ሺህ 300 ተሳታፊዎች ታድመውበታል። በጉባኤው ላይ የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሀገራት እና ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ስድስት የትኩረት አቅጣጫዎችን ይፋ አድርገው ነበር።   የምግብ ስርዓት ስትራቴጂዎችን ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር፣ ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓት አስተዳደር መገንባት፣ በጥናት፣ ዳታ፣ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ ሁሉን አቀፍ የእቅድ ዝግጅት እና ትግበራን ማጠናከር፣ በምግብ ስርዓት ውስጥ የንግዱ ማህበረሰብ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የአጭርና የረጅም ጊዜ የአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ ከትኩረት አቅጣጫዎቹ መካከል ይጠቀሳሉ። ኢንቨስትመንት፣ የበጀት ድጋፍ እና የእዳ አስተዳደር ሌላኛው የትኩረት መስክ ነው። በጉባኤው ላይ 300 ገደማ በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የምግብ ስርዓት ሽግግርን እውን ለማድረግ ቃል መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያመለክታል። በተለይም እ.አ.አ 2030 የማይበገር፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የምግብ ስርዓት መገንባት እንዲሁም ምግብ ለሁሉም የሚለውን ግብ ለማሳካት ጥረት እንደሚያደርጉ ሀገራት ቃል ገብተዋል።   ሁሉን አሳታፊ ነው በሚል አድናቆት ያገኘው ጉባኤው በስርዓት ምግብ ላይ ግንዛቤን ከማሳደግ እና አቅምን ከመገንባት አንጻር ውጤታማ እንደነበር ይነሳል። የምግብ ስርዓት ሽግግር አንገብጋቢና ጊዜ የማይሰጥ ጉዳይ እንደሆነም በጉባኤው ተወስቷል። ኢትዮጵያም በስርዓተ-ምግብ ጉባኤው ላይ የነበራት ተሳትፎ ስኬታማ ነበር። በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ውጤታማ እንቅስቃሴዎችን የሚያሳዩ ልምደችን አቅርባለች። በጉባኤው ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ግብርናን በማዘመን የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና በስርዓተ ምግብ ሽግግር ለማምጣት እየወሰደች ባለው የፖሊሲ እርምጃና ውጤቶች ዙሪያ ገለጻ አድርገውም ነበር። ኢትዮጵያ የኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት፣ ለየስነ ምህዳሩ ተስማሚ የሆኑ የተሻሻሉ ዝርያዎችን፣ አነስተኛ ቴክኖሎጂዎችንና ሌሎች ግብአቶችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለኢኮኖሚው ዕድገት የላቀ አበርክቶ እንዲኖረው እየሰራች መሆኑንም አንስተዋል።   በአረንጓዴ አሻራ፣ በበጋ መስኖ በተለይም በበጋ ስንዴ ምርት እና በሌማት ትሩፋት እየተገኙ ያሉ ውጤቶችን ለጉባኤው አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የስራ እድል ፈጠራን ለማበረታታትም ሆነ በስርዓተ-ምግብ ሽግግር ለማድረግ አዲስና የተለየ የፋይናንስ ሞዴል ያስፋልጋል በማለት በአጽንኦት ተናግረዋል። ዘላቂና አካታች የስርዓተ ምግብ ሽግግር አቅጣጫዎች ጥሩ አፈጻጸም የታየባቸው ቢሆንም በፋይናንስ አቅርቦት፣ በዓለም አቀፍ ትብብር፣ በአየር ንብረት ለውጥና በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመቋቋም በትብብር በመስራት በኩል በርካታ ችግሮች መስተዋላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የገለጹት። በመሆኑም ሀገሮች በስርዓተ ምግብ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በአነስተኛ እርሻ ስር-ነቀል ለውጥ በማምጣት ሽግግሩን ማፋጠን እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፅንኦት አንስተዋል። ለዚህም የሴቶችና የወጣቶች ተሳትፎን እንዲያሳድጉና ለግብርና ቴክኖሎጂ መስፋፋት እንዲሰሩ ጠይቀዋል ። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ-ምግብ ጉባኤ የመጀመሪያውን ጉባኤ መነሻ በማድረግ በተለያዩ አጀንዳዎች ይመክራል። ቀዳሚ ትኩረቱ ከመጀመሪያው ጉባኤው በኋላ የምግብ ስርዓትን አስመለክቶ ያሉ ለውጦች ምንድን ናቸው? የሚለው ነው። በጉባኤው ላይ ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን አስመልክቶ ያገኟቸውን ስኬቶች እና የጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ሪፖርት ያቀርባሉ። በተለይም የምግብ ስርዓት ሽግግሩ ሁለንተናዊነት እና ሁሉን አሳታፊነት ዋንኛ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ሁለተኛው የጉባኤው አጀንዳ በመንግስታት፣ የምግብ አምራቾች፣ የንግድ ማህበረሰቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር ነው። የባለድርሻ አካላት ትብብር መጠናከር የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንዳለው ታምኖበታል። በተጨማሪም ሀገራት እና ተቋማት በሮሙ ጉባኤ የገቧቸው ቃሎች የደረሱበትን ደረጃ የሚገመገም ሲሆን ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎም ይጠበቃል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት እና የኢንቨስትመንት መጠንን መጨመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ጉባኤው ይመክራል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር ስራዎች በአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ፣ አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም እና ሀገር በቀል የፋይናንስ መሰብሰብ አቅምን ማጎልበት ላይ ምክክሮች ይደረጋሉ ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ በሮም በነበረው ጉባኤው ላይ ይፋ ያደረጓቸው ስድስት የትኩረት መስኮች አፈጻጸም ግምገማ ሌላኛው አጀንዳ ነው። በአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ የሚካሄደው ሁለተኛው የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ የሀገራት መሪዎች እና ተወካዮች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ አርሶ አደሮች፣ አምራቾች እና የምግብ ስርዓት ሽግግር ተዋንያንን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። በጉባኤው ላይ ከዋናው ሁነት ጎን ለጎን የምግብ ስርዓት ትራስፎርሜሽን እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን አስመልክቶ በርካታ የጎንዮሽ ስብስባዎች ይደረጋሉ። ኢትዮጵያ በምግብ ስርዓት ሽግግር ያከናወናቸውን ስራዎች አስመልክቶም በጉባኤው ተሳታፊዎች የመስክ ምልከታ ይደረጋል። ኢትዮጵያ በስርዓት ምግብ ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እና በግብርናው ዘርፍ ባደረጋቻቸው ሀገር በቀል ሪፎርሞች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ጉባኤውን እንድታስተናግድ የተመረጥችባቸው ምክንያቶች ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር እየተወጣች ያለው የመሪነት ሚና እና በማደግ ላይ ከሚገኙ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ተምሳሌት የሆነች ሀገር መሆኗ ተመድ ዓለም አቀፉን ከፍተኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ እንዲያደርግ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማሳካት እያከናወነች ባለው ተግባር ዙሪያ ተሞክሮዋን ለዓለም ማህበረሰብ የማስገንዘብ ስራ ታከናውናለች። ተባባሪ አዘጋጇ ጣልያን እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ በምግብ ስርዓት ሽግግር ውጤታማ ተሞክሮ ያላት ሀገር ናት። የደቡብ አውሮፓዊቷ ሀገር ከኢትዮዮጵያ ጋር በመሆን ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን እየሰራችም ትገኛለች። ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎች ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እየጠበቀች ትገኛለች።  
በቻይና ይህም አለ!
Jul 8, 2025 338
  በአብነት ታደሰ በርግጥ ከዓለማችን የጥንት ስልጣኔ ምድሮች አንዷ ናት- ቻይና። በታሪክ ገጾች ‘የግኝት ምድር’(Land of Invention) የሚል ተቀፅላ የሰፈረላት የሺህ ዘመናት ባለታሪክ ሀገር። የጥንት ቻይኖች አያሌ ‘ግኝቶችን’ ለዓለም አካፍለዋል። ወረቀት ፈብርከው ዘመናቸውን ጽፈዋል፣ ማተሚያ ቁስ ፈጥረው አትመዋል፤ ኮምፓስ ፈልስመው አቅጣጫ ጠቁመዋል።በ221 ዓመተ-ዓለም አንድ ወጥ ስርወ መንግስት መስርተው በሀገረ መንግስት የታሪክ ዑደት ከፍታንም ዝቅታንም አይተዋል። በቻይና አያሌ ስርወ መንግስታት ተፈራርቀዋል። ቻይናውያን ክፉውንም ደጉንም ችለው አልፋዋል። የሕዝቡ ጽናት፣ ጥበብ፣ ቱባ ባህል፣ ታሪክና ብልሃት በቻይና ግንብ ይመሰላል። ግንቡም ዝም ብሎ የጡብ ክምር አይደለም፤ የመሰረተ-ጽኑነታቸው ትዕምርት(symbol) እንጂ። ሲሶውን ሕዝቧ በያንግትዝ ወንዝ ተፋሰስ ጉያ አቅፋ፣ ጥንተ ማንነቷን ሸክፋ ዕልፍ ዘመናትን ተሻግራለች። የቻይና ስርወ መንግስታት ከስመው የዛሬዋ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ ቻይና ከተመሰረተች ገና አንድ ምዕተ ዓመቷ ነው። ቅድመ ልደተ ክርስቶት በ221 ዓመተ-ዓለም የተመሰረተው ወጥ-ስርዎ መንግስት በመልከ ብዙ ምክንያቶች ተዳከመ። በፈረንጆቹ 1912 የመጨረሻው የቻይና ስርዎ መንግስት ተንኮታኮተ። ዘመናዊቷ የቻይና ሪፐብሊክ በዚህ ዘመን ተመሰረተች። ዳሩ ለውጡ አልጋ በአልጋ አልሆነም። ለሺህ ዘመን የጽኑ ስርዓተ መንግስት ባለቤቷ ሀገር ቻይና በአስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት ታመሰች። ወረራንም፣ ዕልቂትንም አስተናገደች። በዘመኑ ማኦ ዘዶንግ የሚባል ባለራዕይ መሪ በቻይና ምድር ተነሳ። አርቆ አሰበ፤ ሀሳቡንም አሰረጸ፤ በዓላማ ጸንቶ ክፉ ዘመን ተሻገረ። ማኦ እና ተከታዮቹ ለቻይና ትንሳኤ ታተሩ። በጽናት ታገሉ። ለመስዕዋትነት ቆርጠው ተነሱ፤ ዋጋም ከፈሉ። በአውሮፓዊኑ ዘመን አቆጣጣር በ1949 የዛሬዋን የቻይና ሕዝባዊ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ መሰረተ። ሃሳቡን ወደ ፖሊሲ ቀየረ፤ ተገበረውም። ቻይናን በኢንዱስትሪና ግብርና ምርት በንቅናቄ የማስፈንጠር ፕሮግራምንም (Great Leap Forward) ገቢራዊ አደረገ። ሆኖም ፖሊሲው በአንዴ ፍሬ አላፈራም። በወቅቱ በተፈጥሯዊና በሌሎች ምክንያቶች ቻይና በረሀብ ጠኔ ተመታች። ቻይናዊያን ተራቡ፤ ጎረቤት ሀገራትን ደጅ ጠኑ፤ ታላቁን ረሀብ መሻገር ያልቻሉ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቻይናዊያን በረሀብ አለቁ። በቻንግሻ የሚገኘው የማኦ ዘዶንግ ግዙፍ ሐውልት መራራ ጽዋን ተጎነጩ። የሀገሪቷ መሪ ማኦ ዘዶንግ በወቅቱ ፈተና ተስፋ ሳይቆርጥ ሀገር አሻጋሪ ፖሊሲውን ገቢራዊ አደረገ። ልመናን ለትውልድ ላለማውረስ፣ ንቅዘትን(ሙስናን) ነውር የሚያደርግ ስርዓት አጸና። ስራን ወንጌል፤ ሙስናን ወንጀል ያደረገ ጽኑ ስርዓተ መንግስት ገነባ። ከራሷ አልፋ ለዓለም የተረፈችዋን የዛሬዋን ቻይና በጽኑ መሰረት ላይ አነበረ። የዛሬዋ ቻይና ከዓለማችን ቁንጮ ልዕለ ሃያል ሀገራት አንዷ ናት። ከራሷ አልፋ ለዓለም ተርፋለች፤ የቻይና ቴክኖሎጂ ምጥቀትና ርቀት ዓለም ጉድ አሰኝቷል። በቅርቡ ሀገረ ቻይናን ከጎበኙ ጋዜጠኞች አንዷ ሆኜ ‘መልክዓ ቻይና’ን በወፍ በረር ቃኘሁ። በዚህ ማስታወሻዬ በቻይና የቴክኖሎጂ ልህቀትና ምጥቀት ላይ ብቻ አተኩራለሁ። ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ህዝብ ባላት፣ በ14 ሀገራት በምትዋሰነው፣ በአንድ ኮሚኒስት ፓርቲ በምትመራው ሀገር ቻይና በነበረኝ የ15 ቀናት ቆይታ ቻይና እንደ ጥንተ ታሪኳ ሁሉ በዘመኑ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ላይ ያላትን የመራቀቅ ጥግ ታዘብኩ። ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን የመቅደም እሽቅድድሟ ‘አጃይብ’ ያሰኛል። በሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና በማዕከላዊ ቻይዋ በምትገኘው የሁናን ግዛት ዋና ከተማ ቻንግሻ ምልከታዬ ቻይና ’ከተባለላት በላይ’ የቴክኖሎጂ ምጥቀቷ አስደንቆኛል። ምናልባትም የመጀመሪያ ጉዞዬ መሆኑም ነገሩን በአንክሮት እንድመለከት ሳያስገድደኝ አልቀረም። የሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከ22 ሚለዮን የሚልቅ ህዝብ በጉያዋ የታቀፈችው ታላቋ ቤጂንግ ከተማ ከዓለማችን ግንባር ቀደም የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህል፣ የቱሪዝምና የዲፕሎማሲ ማዕከላት አንዷ ናት። የአዲስ አበባ እህት ከተማ በዚህ ወቅት ሞቃታማ አየር ጸባት አላት። ቤጂንግ የ21ኛው ክፍል ዘመን የኪነ ህንፃና ክትመት ቴክኖሎጂ ያበበች ብቻ አይደለችም፤ ይልቁኑም በዛፎች ሀመልማላዊ ገጽታ የተላበሰች ውብ መዲና እንጂ። በሕንፃዎችም፣ በዛፎችም የተደነነች ከተማ። በተፈጥሮ የበቀሉ የሚመስሉ ሰማይ ታካኪ ሕንጻዎች፤ የመንገድ መሰረተ ልማት ስፋት፣ ጽዳትና ጥራት ‘ኩልል’ ያለች፣ ‘ምልል’ የምታደርግ ከተማ ያደርጋታል። ቤጂንግ ከተማ ከዘመናችን አስደናቂ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አንዱ በሆነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ) ሕይወትና ኑሮን እንዴት እንዳቃለለ የቤጂንግ የዕለት ከዕለት ክዋኔ ሁነኛ ማሳያ ነው። ቻይኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ተጠበዋል፤ መጠበብ ብቻም ሳይሆን ኑባሬያቸውን ሰው ሰራሽ አስተውሎት መር አድርገዋል። ከሮቦት መስተንግዶ እስከ ሰው ሰራሽ ፀሐይ መራቀቅ ይስተዋላል።   ካረፍኩበት ሆቴል (15ኛ ወለል ላይ ከሚገኘው መኝታ ክፍሌ) ሆኜ ያዘዝኩት ምግብ በቅጽበት አስተናጋጇ ‘ከች’ ብላ ትደውላለች። ፍጥነቷ ስትገረም፤ አስተናጋጆች ሮቦቶች መሆናቸውን ስትመለከት ይበልጥ ትደነቃለለህ። በክፍሌ ውስጥ ማብሪያ ማጥፊያ ስጫን መጋረጃው ሲከፈት መደንገጤን አልሸሽግም፣ ከምሽቱ 3 ሰዓት ፀሐይ አለመጥለቋን ስመለከት ‘የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ወጣች እንዴ?’ ማለቴ አልቀረም። በነገራችን ላይ የቻይና የሰው ሰራሽ ፀሐይ ሳይንሳዊ ፈጠራ ሁለት ግዜ ተሞክሮ ያለምንም እንከን እንደሚሰራ ነግረውናል። የሰው ሰራሽ ፀሐዩ ሃይድሮጅን እና ዱተሪየም ጋዞችን እንደ ሀይል ማመንጫ ነዳጅነት በመጠቀም ንጹህ ኢነርጂን ለማመንጨት ታስቦ ዲዛይን እንደተደረገና ሰው ሰራሽ ፀሐይ በርሐን ከተፈጥሮ ፀሐይ 13 እጥፍ ያክል ሙቀት እንደሚያመነጭም ሰምተን ተደንቀናል። የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ፕሮጀክት የሥራ ሰዓትን ከ13 ሰዓት ወደ 24 ሰዓት ለመጨመርና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብ የሰነቀ ነው። በቻይና በሰዉ ቅርፅ የተሰሩ ሮቦቶች በእግር ኳስ ጨዋታዎች ተወዳጅነት አትርፈዋል። ቤጂንግ የሚገኘው ሂዩማኖይድ የተሰኘ የሮቦት ቡድን የሰራቸው ሮቦቶች አመርቂ ውጤት ከራቀው የሀገሪቷ እግር ኳስ ቡድን ይልቅ የሀገሬውን ቀልብ እንደሳቡ ይነገራል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት በታገዘ የሮቦቶች ውድድር አያሌ ቻይናዊያን ይታደማሉ። ሮቦቶቹ በጨዋታ መሐል ቢወድቁ በራሳቸውን ይነሳሉ፤ ቢጎዱም ከሜዳ የሚወጡበት ስርዓት ተዘርግቷል። የታላቋ ቻይና ሰዎች ቴክኖሎጂን ከችግር መፍቻነት ወደ መዝናኛነትም አልቀውታል። በሀገራችን እንደ አዲስ ቴክኖሎጂ በንግዱ ስርዓት ውስጥ እየተዋወቀ ያለው የፈጣን ምላሽ መለያ ወይም ኪው አር ኮድ(Quick Response code) በቻይና ዕለታዊ ከዋኔዎች ቅንጦት አይደለም። በቻይና ማንኛውም ግልጋሎት በዚህ በዲጂታል ስርዓት ይከወናል። እንደሌሎች ስልጡን ሀገራት ሁሉ በንክኪ የሚደረግ ገንዘብ ዝውውር ቀርቷል። በቤጂንግ ጎዳናዎች በኪው አር ኮድ(QR Code) በሚንቀሳቀሱ ሞተር ሳይክሎችን በየመንገዱ ተሰድረዋል፤ የፈለገ መንገደኛ ሳይክሎችን በመጠቀም ወደ ፈለገበት ስፍራ ተንቀሳቅሶ ክፍያውን በኪው አር ኮድ ከፍሎ ይሄዳል። ሌላውም እንዲሁ። በአዲስ አበባ መኖሪያ ሰፈሬ የነበሩ ሳይክሎኝ ከደጃችን ደብዛቸው እንደጠፋ ሳስብ በቻይኖች ብልሃት፣ ታማኝነትና የከተሜነት ልህቀት ቀናሁ። በርግጥ በቻይና ኪው አር(QR) ኮድ ለተገለገልንበት መክፈያ ብቻ ሳይሆን ለልመናም መዋሉን ሲመለከቱ ፈገግ ሊሉ ይችላሉ። በቻይና ይህም አለ በማለት። በርግጥ በቤጂንግ የሰው እጅ ከሚያይ ይልቅ ጆሮቸውን ቢቆጥርጣቸው የሚሰሙ የማይመስሉ አዛውንቶች ሳይቀር በስራ ላይ ተጠምደው ይስተዋላሉ። ከቻይናውያን ጋር ለመግባባት በተለይም በንግድ ማዕከላት የቻይንኛ ቋንቋ መረዳት ግድ ይላል። “ሃው ማቺ፣ ጉዳ ጉዳ፤ ሺሼ፣ ኢ፣ አር…” እና መሰል ቃላት ማወቅ ይበጃል። ከዚህ ባለፈ በምልክት መግባባት አልያም በቋንቋ ተርጓሚ መተግበሪያ መጠቀም ያሻል። የቻይና ሰራሽ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምርቶች በራሳቸው ብራንድ፣ ቋንቋና መልክ እየተመረቱ በተመጣጣሽ ዋጋ ለህዝቦቿ ተደራሽ እየተደረጉ ነው። የቻይና የራስ-በቅነት ጥረት ያስቀናል። በቴክኖሎጂ፣ በባሕልና በኢኮኖሚ ተጽዕኖ ተላቀው በራሳቸው ለመቆም የሄዱበት ርቀት ግሩም ነው። ግብይቶች በራሳቸው ገንዘብ ብቻ ይከወናል። በወቅቱ ምንዛሬ አንድ የአሜሪካ ዶላር ሰባት የቻይና ገንዘብ(ዩዋን) ነው። ከምዕራባዊያን ማህበራዊ ትስስር ገጾች(ለምሳሌ ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክ) በሕግ በማገድ የራሳቸውን መተግበሪያ አበልጽገው ገቢራዊ አድርገዋል። ‘ዊቻት’ የተሰኘው መተግበሪያ ሁሉም ቻይናውያን መገልገያ ነው።   ከቤጂንግ ሌላ ያስደነቀችኝ ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከተማ ነች። ቻንግሻ ስመ-ብዙ ነች። ከሶስት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ ጠገቧ የሁናን ግዛት ርዕሰ መዲና ቻንግሻ ‘የከዋክብት ከተማ’ ትሰኛለች። በነገራችን ላይ ማኦ ዘዶንግ ትውልዱ ሁናን ግዛት ውስጥ ነው። ቻንግሻ በስራ ከተማነቷ ‘የማታንቀላፋው መዲና’ ትባላለች። በመዝናኛ ስፍራነቷ ‘የተዝናኖት መነሃሪያ’ የሚል ተቀጥላ ስም አላት። ‘የሚዲያ ጥበብ’ ስፍራም ትሰኛለች። በኢንዱስትሪ፣ በጥንታዊ ሐውልቶች፣ አብያተ መቅደሶች፣ ታሪካዊ ስፍራዎች መገኛ በመሆኗ በቱሪስቶች ተወዳጅ ከተማ ናት። ትናንትና ዛሬን ያዋደደች፣ ታሪክና ባህል ባዛነቀችዋ ቻንግሻ የአምስት ቀናት ቆይታዬ ብዙ ገጽታዋ አስደምሞኛል። የሻንግ ወንዝን ተንተርሳ፣ በተራራማ፣ በሜዳማና ኮረብታማ መልክዓ ምድር በማዛነቅ የተቆረቆረች በመሆኗ የስብት ማዕከል ሆናለች። እንደ ቤጂንግ በደን የተከበበች፣ በዘመነኛ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች እና በታሪካዊ ኪነ ሕንጻዎች የተጌጠች ከተማ ናት። ከዚህ ባሻገር የአምራች ኢንዱስትሪዎች መናገሻም ናት። የምቹ ከተሜነትና ጠንካራ የስራ ባህል በግላጭ የሚስተዋልባት ከተማ። የዓለማችን ገዙፉ በጣም ሞቃታማ አየር ጸባይ ባላት ቻንግሻ ሌት ከቀን ይሰራል። ፋብሪካዎቿ አይተኙም። ሌትና ቀኑ የሚታወቀው በሰዓት ብቻ እንጂ የስራና የንግድ ድባቡ እኩል ነው። ብርሃናማዋ ቻንግሻ ‘የቻይዊያን መስቀል’ በተሰኘው በቀይ በተቀለመው መስቀልም ትታወቃለች። በርግጥ ከዓለማችን ግዙፍ ማማዎች አንዱ የሆነው ሕንጻም መገኛ ናች። በጥቅሉ የቻይና ጉብኝት ትዝብቴ የገናና ታሪክ ባለቤቷ ሀገር ከባድ ውጣ ውረዶችን አልፋ ዛሬ ዓለምን እየቀደመች መሆኑን ሳስብ፤ እንደቻይና ሁሉ የሺ ዘመናት ገናና ታሪክና አኩሪ ገድል ያላት ኢትዮጵያስ የሚል ተጠየቅ እንዳውጠነጥን አድርጎኛል። ቻይናዊያን የዘመን የፈተና ቋጠሮዎቻቸውን ፈታተው ከዛሬ ከፍታ ሰገነት ላይ ወጥተዋል። ከዛሬም በበለጠ ነገን በጽኑ መሰረት ላይ እየገነቡ ነው። እኛስ? ብዬ ሳስብ በቁጭትና በተስፋ ተዋጥኩ! ሰላም!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም