ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የተረከብናቸው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርሶች ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው
Nov 19, 2025 42
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ ዛሬ ከጀርመናውያን ቤተሰቦች የተረከብናቸው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርሶች በተመሳሳይ በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ። በጀርመናውያን ቤተሰቦች እጅ የነበሩ 12 ልዩ ልዩ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቅርሶችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ተረክቧል፡፡   በርክክብ ስነ ስርዓቱ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙዔል ክፍሌ(ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ ፈርዲናንድ ቮን ወይሄ(ዶ/ር) ተገኝተዋል። የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ቅርሶች እኤአ 1921-1928 በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ልዩ መልዕክተኛ ለነበሩት ፈርቲዝ ዌይስ በንግስት ዘውዲቱ እና አጼ ኃይለሥላሴ በስጦታ ተበርክተው የነበሩ እና በግል የተገዙ ናቸው ብለዋል፡፡ አሁን ላይ በህይወት የሌሉት የፈርቲዝ ዌይስ የልጅ ልጅ ራሞርና ቤተሰቦቹ በራሳቸው ተነሳሽነት በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ በኩል ጥንታዊ ቅርሶቹን መልሰዋል ነው ያሉት፡፡ ቅርሶቹ ከቱሪዝም መስህብነታቸው ባሻገር ታሪክን ወደ ቤቱ የመለሱና የሀገራቱን ወዳጅነት በግልጽ ያሳየ መሆኑን ጠቁመው፤ ድርጊቱ በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው ብለዋል።   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባበቂ ፕሬዚዳንት ሳሙዔል ክፍሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በስጦታ የተበረከቱም ሆነ የተወሰዱ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቅርሶችን እንዲመለሱ በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡   በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ ፈርዲናንድ ቮን ወይሄ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቅርሶቹ የተመለሱት ያለምንም ጣልቃ ገብነት በቅርሱ ባለቤት ቤተሰቦች መልካም ፈቃድ ነው ብለዋል፡፡ ይህም የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚያጠናክር ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡   ከተመለሱት ቅርሶች መካከል ጎራዴ፣ ዘውድ፣ አክሊል፣ ስዕሎችና ሌሎች የኢትዮጵያን ማንነት የሚገልጹ ቅርሶች እንደሚገኙበት የገለጹት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ዳይሬክተር ዮሃንስ አድገህ(ዶ/ር) ናቸው። ቅርሶቹ ከቱሪዝም መስህብነት ባሻገር ለጥናትና ምርምር ግብዓት ሆነው እንደሚያገለግሉም ተናግረዋል፡፡   በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ልዩ መልዕክተኛ የነበሩት ፍርቲዝ ዌይስ የልጅ ልጅ ፕሮፌሰር ራሞን ዌይስ በበኩላቸው፤ ቅርሶቹ ከግለሰብ ይልቅ ለኢትዮጵያ ይበልጥ ይጠቅማሉ ብለን እንደቤተሰብ መክረን መልሰናል ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያዩ
Nov 19, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ባለፈው ዓመት ወደ ማሌዥያ ኦፊሴላዊ ጉብኝት ካደረኩኝ አንድ ዓመት በኋላ፣ የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂምን በኢትዮጵያ ተቀብያለሁ ብለዋል።   ይህ የጉብኝት ልውውጥ ጥልቅ አጋርነታችንን የሚመሰክር ሲሆን ይህም በርካታ ቁልፍ ሰነዶችን በመፈረም ተጠናክሯል ነው ያሉት። የመግባቢያ ሰነዶቹ በቱሪዝም፣ በጤና፣ በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት፣ በኳላ ላምፑር ከተማ ምክር ቤት እና በአዲስ አበባ አስተዳደር የትብብር መስክ ላይ ያተኮሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል።   ባደረግነው የሁለትዮሽ ውይይት፣ ትብብራችንን የበለጠ ለማጠናከር እና ለማስፋት ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት አረጋግጠናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በመልዕክታቸው።
ኢትዮጵያ የተወሰዱባትን 12 ውድ ቅርሶች ተረከበች
Nov 19, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በ1920ዎቹ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ 12 ውድ ቅርሶችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት እና ምርምር ተቋም ተቀብሏል። ቅርሶቹ የፕሮፌሰር ራሞን አያት እንዲሁም በ1920ዎቹ በኢትዮጵያ የጀርመን ልዑክ በነበሩት ፍራንዝ ዊስ የአገልግሎት ዘመን ከኢትዮጵያ የተወሰዱ ሲሆን፣ ፍራንዝ እና ባለቤታቸው ሄድዊግ ገንዘብ ከፍለው የሰበሰቧቸው ናቸው። ለዩኒቨርሲቲው ከተበረከቱት ውድ ቅርሶች ውስጥ ዘውድ፣ ጋሻ፣ ጎራዴ፣ ዝናር፣ ስዕሎች እንዲሁም ከራስ ተፈሪ መኮንን የተበረከቱ ስጦታዎች ይገኙባቸዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ቅርሶቹ የኢትዮጵያ ሃብቶች ከመሆናቸው በተጨማሪ ለጥናትና ምርምር በግብዓትነት የሚያገለግሉ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በመላው ዓለም በግለሰቦች እጅ እና በተቋማት ውስጥ የሚገኙና የኢትዮጵያ ታሪክ አስረጂ የሆኑ ጥንታዊ ቅርሶች ወደ ሃገር እንዲመለሱ የማድረጉ ጥረትም ይቀጥላል ማለታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።
የሚታይ
የተረከብናቸው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርሶች ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው
Nov 19, 2025 42
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ ዛሬ ከጀርመናውያን ቤተሰቦች የተረከብናቸው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርሶች በተመሳሳይ በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ። በጀርመናውያን ቤተሰቦች እጅ የነበሩ 12 ልዩ ልዩ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቅርሶችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ተረክቧል፡፡   በርክክብ ስነ ስርዓቱ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙዔል ክፍሌ(ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ ፈርዲናንድ ቮን ወይሄ(ዶ/ር) ተገኝተዋል። የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ቅርሶች እኤአ 1921-1928 በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ልዩ መልዕክተኛ ለነበሩት ፈርቲዝ ዌይስ በንግስት ዘውዲቱ እና አጼ ኃይለሥላሴ በስጦታ ተበርክተው የነበሩ እና በግል የተገዙ ናቸው ብለዋል፡፡ አሁን ላይ በህይወት የሌሉት የፈርቲዝ ዌይስ የልጅ ልጅ ራሞርና ቤተሰቦቹ በራሳቸው ተነሳሽነት በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ በኩል ጥንታዊ ቅርሶቹን መልሰዋል ነው ያሉት፡፡ ቅርሶቹ ከቱሪዝም መስህብነታቸው ባሻገር ታሪክን ወደ ቤቱ የመለሱና የሀገራቱን ወዳጅነት በግልጽ ያሳየ መሆኑን ጠቁመው፤ ድርጊቱ በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው ብለዋል።   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባበቂ ፕሬዚዳንት ሳሙዔል ክፍሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በስጦታ የተበረከቱም ሆነ የተወሰዱ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቅርሶችን እንዲመለሱ በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡   በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ ፈርዲናንድ ቮን ወይሄ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቅርሶቹ የተመለሱት ያለምንም ጣልቃ ገብነት በቅርሱ ባለቤት ቤተሰቦች መልካም ፈቃድ ነው ብለዋል፡፡ ይህም የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚያጠናክር ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡   ከተመለሱት ቅርሶች መካከል ጎራዴ፣ ዘውድ፣ አክሊል፣ ስዕሎችና ሌሎች የኢትዮጵያን ማንነት የሚገልጹ ቅርሶች እንደሚገኙበት የገለጹት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ዳይሬክተር ዮሃንስ አድገህ(ዶ/ር) ናቸው። ቅርሶቹ ከቱሪዝም መስህብነት ባሻገር ለጥናትና ምርምር ግብዓት ሆነው እንደሚያገለግሉም ተናግረዋል፡፡   በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ልዩ መልዕክተኛ የነበሩት ፍርቲዝ ዌይስ የልጅ ልጅ ፕሮፌሰር ራሞን ዌይስ በበኩላቸው፤ ቅርሶቹ ከግለሰብ ይልቅ ለኢትዮጵያ ይበልጥ ይጠቅማሉ ብለን እንደቤተሰብ መክረን መልሰናል ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያዩ
Nov 19, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ባለፈው ዓመት ወደ ማሌዥያ ኦፊሴላዊ ጉብኝት ካደረኩኝ አንድ ዓመት በኋላ፣ የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂምን በኢትዮጵያ ተቀብያለሁ ብለዋል።   ይህ የጉብኝት ልውውጥ ጥልቅ አጋርነታችንን የሚመሰክር ሲሆን ይህም በርካታ ቁልፍ ሰነዶችን በመፈረም ተጠናክሯል ነው ያሉት። የመግባቢያ ሰነዶቹ በቱሪዝም፣ በጤና፣ በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት፣ በኳላ ላምፑር ከተማ ምክር ቤት እና በአዲስ አበባ አስተዳደር የትብብር መስክ ላይ ያተኮሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል።   ባደረግነው የሁለትዮሽ ውይይት፣ ትብብራችንን የበለጠ ለማጠናከር እና ለማስፋት ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት አረጋግጠናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በመልዕክታቸው።
በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ችግር ፈቺ ፈጠራና መፍትሔዎችን እያስገኙ ነው
Nov 19, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ችግር ፈቺ ፈጠራና መፍትሔዎችን እያስገኙ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ፡፡ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንትን በማስመልከት የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መንግስት የኢንተርፕርነርሽፕ ስነ ምህዳሩን ምቹ ለማድረግ በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ ይገኛል። ባለፉት ሰባት ዓመታት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ ምህዳሩን ማስፋት የሚያስችሉ አሰራሮችና ተቋማት ሪፎርምና አጀንዳ ቀረፃ ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም መንግስት በመፍጠርና በመፍጠን አገልግሎቶችን በመስጠት ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡   የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከተቋቋመ ጀምሮ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ከግለሰብ እስከ ተቋማት ድረስ እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ኢንተርፕርነሮችን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ብቁና ንቁ ተወዳዳሪ በማድረግ ሀገራቸውን ከድህነት የሚያወጡ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ችግርን መሰረት ያደረጉ መፍትሄ ሰጪ ፈጠራዎችን እያስገኙ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ኢትዮጵያን የምንገነባበትና ወደ ፊት የምናስፈነጥርበት፤ ዓለም ከደረሰበት ደረጃ ለማድረስ የምንጠቀምበት መድረክ ነው ሲሉም ገልዋል፡፡

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
አመራሩ በመፍጠር እና በመፍጠን ለልማትና ለህዝብ ተጠቃሚነት ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል
Nov 19, 2025 66
አሶሳ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በየደረጃው ያለው አመራር በመፍጠር እና በመፍጠን ለሀገር ልማትና ለህዝብ ተጠቃሚነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር ተናገሩ። ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል በተለይም የአመራሩ ብቃትና ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በየደረጃው ያለው አመራር በመፍጠር እና በመፍጠን ለሀገር ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት የበለጠ ለመስራት ሊዘጋጅ እንደሚገባ አስገንዝበው የስልጠናው አላማም ይሄው ነው ብለዋል። በስልጠናው የግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ የቱሪዝም፣ የከተማ ልማት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችን ለማስቀጠል የዳበረ ውይይት የሚደረግበት መሆኑንም ተናግረዋል። በስልጠናው ተሞክሮዎችና ልምዶችን በመጋራት አመራሩ በጋራ ለላቀ ስኬት ለመስራት የሚዘጋጅበት ስለመሆኑም ገልጸዋል። የአመራሮቹ ስልጠና ለተከታታይ ስምንት ቀናት የሚሰጥ መሆኑም ታውቋል።  
አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነትን እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጠናከር አለበት
Nov 19, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሠራ በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ የአመራር አባላት ስልጠና በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በስልጠናው የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡   ስልጠናው “በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለሚቀጥሉት ስምንት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል። በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ገለጻ፤ የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት ይሠራል ብለዋል። አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነትን እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጠናከር እንደሚገባውን ተናግረዋል።   የስልጠናው ዓላማም በአመራሩ መካከል የበለጠ መቀራረብና የአስተሳሰብ አንድነትን መፍጠር እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጎልበት መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም አገልጋይና ሁለገብ የሆነ አመራር መፍጠር ከስልጠናው ዓላማዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ስልጠናው በተለያዩ ሀገራዊ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በማተኮር እንደሚሰጥም ተናግረዋል።   በዚህም ስልጠናው በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣ የገጠር፣ የመዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ የኢንዱስትሪ እና የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ እንዲሁም የከተማ ልማት በሚል ርዕሶች ላይ እንደሚያተኩር ገልጸዋል፡፡ ስልጠናው የአመራሩን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነባ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በስልጠናው ከሁለት ሺህ በላይ የፌዴራልና የከተማዋ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር አባላት እንደሚሳተፉና ጎን ለጎንም የተግባርና የመስክ የልማት ስራ ጉብኝቶች እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን- የፖሊስ አባላት
Nov 19, 2025 63
ቦንጋ፤ ህዳር 10/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፖሊስ አመራርና አባላት ተናገሩ። በክልሉ "ከጂኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሃሳብ በየደረጃው ለሚገኙ የፖሊስ አመራርና አባላት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የፖሊስ አመራርና አባላትም የተሰጠው ስልጠና በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት ህዝብን ከማገልገል ባለፈ በሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የተሻለ ግንዛቤ ለመያዝ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል ኮማንደር እታለማው ተፈራ፣ ኢንስፔክተር አባይነህ አልዬ እና ምክትል ኢንስፔክተር አንድነት አበራ፤ የተሰጠው ስልጠና ወቅታዊ ሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮችን በመረዳት ለላቀ ህዝባዊ አገልግሎት የሚያዘጋጅ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህም ባለፈ ወቅታዊ ሁኔታዎችን በአግባቡ በመረዳት በዚሁ ልክ የፓሊስ አባላት አቅማችንን ማሳደግ ያለብን መሆኑን የተገነዘብንበት ነው ብለዋል። በሁሉም መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ከምንም በላይ የህዝብን ሰላም ማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተው ለዚህም የፖሊስ አባላት የላቀ ሃላፊነት ይጠበቅብናል ለዚህም ተዘጋጅተናል ሲሉ ተናግረዋል። የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን በማለትም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ የፖሊስ አባላት የህዝብና የሀገር ወገንተኝነታቸውን በተግባር በማሳየት ለሰላምና ለልማት ዘብ መቆም እንዳለባቸው ገልጸዋል። በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተመዘገበው ስኬት ውስጥ የፖሊስ ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተው በቀጣይም ይህንኑ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ ሀገር በመገንባት ሂደት በየሙያ መስኩ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አንስተው የፖሊስ አባላት የክልሉን ሰላምና ልማት በዘላቂነት ለማስቀጠል እንዲተጉ አሳስበዋል። የክልሉ መንግስት የፖሊስን አቅም በቴክኖሎጂ እና በስልጠና ጭምር ለማጠናከር የሚሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው ስልጠና ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተሞች የተወጣጡ የፖሊስ አባላትና አመራሮች ተሳትፈዋል።  
በክልሉ የአመራሩን አቅም በማጎልበት ልማታዊ እመርታዎችን የማስቀጠል ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Nov 19, 2025 56
ጋምቤላ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም በማጎልበት እየተመዘገቡ ያሉ ልማታዊ እመርታዎችን የማስቀጠል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ። ’’በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ’’ በሚል መሪ ሃሳበ በጋምቤላ ክልል ሁለተኛው ዙር የከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ ከሰዓት በኋላ በጋምቤላ ከተማ ተጀምሯል። በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሽኔ አስቲን በዚሁ ወቅት፤ እንደ ሀገር እተመዘገቡ የሚገኙ የልማት እመርታዎችን ማፋጠን ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በክልሉ የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችና ትሩፋቶችን ይበልጥ በማፍጠን የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የአመረሩን የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም የማጎልበቱ ተግባር ተጠናከሮ ይቀጥላል ብለዋል። በመደመር መንግሥት በግብርና፣ በገጠር ትራንስፎረሜሽን፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተሞች ልማት እና በሌሎችም ዘርፎች የታለመውን ሀገራዊ ለውጥ በተመሳሳይ ደረጃ ለመፈጸም የአመራሩን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት የመገንባቱ ሂደትም እንዲሁ። ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሕዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚቆይ ተመልክቷል።
ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ ነው
Nov 18, 2025 128
‎ሀዋሳ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በብልፅግና ፓርቲ የሥልጠና መድረክ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ። በአዳማ በተካሄደው የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሥልጠና ላይ የተሳተፉ የሲዳማ ክልል አመራሮች የጋራ የውይይት መድረክ ዛሬ ማምሻውን ተካሄዷል፡፡   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በፓርቲው የተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ በክልሉ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ፍጥነትንና ፈጠራን በማከል ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን የበጀት ዓመቱን የሥራ ዕቅድ በመከለስ ውይይት እየተደረገበት እንደሚገኝ ገልጸዋል።፡ በዚህም በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት፣ በግብርናና ገጠር ልማትና በሌሎች የትኩረት መስኮች የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ ተግባቦት መፍጠር እንደተቻለ ጠቁመዋል፡፡ ይህንን ገቢራዊ ለማድረግም በክልሉ ያሉ የሰላምና ጸጥታና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎችን በመጠቀም እንደሚሰራ ተናግረዋል።   ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠልም የጊዜ፣ የጉልበትና የበጀት ብክነትን በማስቀረት ባጠረ ጊዜ ውስጥ የተነደፉ ዕቅዶችን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም አስረድተዋል፡፡ ሰላምና ልማት ወዳዱን ህዝብ እንዲሁም ባለሀብቱን በማስተባበርም የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በተሻለ ሁኔታ እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል። ገቢን አሟጦ በመሰብሰብም የተሻለ የመፈፀም አቅም በመፍጠር ዕቅዶችን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወንም አቅጣጫ መቀመጡን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ይሰራሉ
Nov 18, 2025 172
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና አዘርባጃን የፓርላማ፣ የህዝብ ለህዝብና የኢንቨስትመንት ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ታገሰ ጫፎ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኤልቺን አሚርባዮቭን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።   በውይይታቸውም የሁለቱን አገራት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ህዝብ ለህዝብ ትስስር በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የሁለቱ ሀገራት ፓርላማዎች ትስስር የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ለማጠናከር አጋዥ መሆኑ ተገልጿል።   በዚሁ ወቅት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ እንዳሉት፤ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ለረጅም ዓመታት የዘለቀና እየተጠናከረ የመጣ ነው። ሁለቱ ሀገራት ሲቪል ሰርቪሱን ለማጠናከር እንዲሁም በትምህርት ዘርፍ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርጓትን ተግባራት እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቅሰው፤ የአዘርባጃን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሰማሩ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።   አፈ ጉባዔው አዘርባጃን ኮፕ 29ን ማስተናገዷን አንስተው ኢትዮጵያ የኮፕ 32ን በውጤታማነት እንድታስተናግድ አዘርባጃን ያላትን ልምድና ተሞክሮ እንድታጋራ ጠይቀዋል። የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኤልቺን አሚርባዮቭ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ያላቸውን ትስስር የበለጠ ለማጠናከር እንሰራለን ብለዋል።   አዘርባጃን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ለዓመታት የዘለቀ ግንኙነት፣ የህዝብ ለህዝብ፣ የባህልና የንግድ ትስስር ለማጠናከር እንደሚሰራ ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማስተናገድ በመመረጧ እንኳን ደስ ያላችሁ ያሉት አምባሳደር ኤልቺን፤ አዘርባጃን ኮፕ 32 በስኬት እንዲጠናቀቅ ሀገራቸው ያላትን ልምድና ተሞክሮ ለማጋራት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
ፖለቲካ
አመራሩ በመፍጠር እና በመፍጠን ለልማትና ለህዝብ ተጠቃሚነት ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል
Nov 19, 2025 66
አሶሳ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በየደረጃው ያለው አመራር በመፍጠር እና በመፍጠን ለሀገር ልማትና ለህዝብ ተጠቃሚነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር ተናገሩ። ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል በተለይም የአመራሩ ብቃትና ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በየደረጃው ያለው አመራር በመፍጠር እና በመፍጠን ለሀገር ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት የበለጠ ለመስራት ሊዘጋጅ እንደሚገባ አስገንዝበው የስልጠናው አላማም ይሄው ነው ብለዋል። በስልጠናው የግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ የቱሪዝም፣ የከተማ ልማት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችን ለማስቀጠል የዳበረ ውይይት የሚደረግበት መሆኑንም ተናግረዋል። በስልጠናው ተሞክሮዎችና ልምዶችን በመጋራት አመራሩ በጋራ ለላቀ ስኬት ለመስራት የሚዘጋጅበት ስለመሆኑም ገልጸዋል። የአመራሮቹ ስልጠና ለተከታታይ ስምንት ቀናት የሚሰጥ መሆኑም ታውቋል።  
አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነትን እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጠናከር አለበት
Nov 19, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሠራ በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ የአመራር አባላት ስልጠና በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በስልጠናው የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡   ስልጠናው “በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለሚቀጥሉት ስምንት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል። በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ገለጻ፤ የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት ይሠራል ብለዋል። አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነትን እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጠናከር እንደሚገባውን ተናግረዋል።   የስልጠናው ዓላማም በአመራሩ መካከል የበለጠ መቀራረብና የአስተሳሰብ አንድነትን መፍጠር እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጎልበት መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም አገልጋይና ሁለገብ የሆነ አመራር መፍጠር ከስልጠናው ዓላማዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ስልጠናው በተለያዩ ሀገራዊ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በማተኮር እንደሚሰጥም ተናግረዋል።   በዚህም ስልጠናው በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣ የገጠር፣ የመዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ የኢንዱስትሪ እና የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ እንዲሁም የከተማ ልማት በሚል ርዕሶች ላይ እንደሚያተኩር ገልጸዋል፡፡ ስልጠናው የአመራሩን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነባ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በስልጠናው ከሁለት ሺህ በላይ የፌዴራልና የከተማዋ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር አባላት እንደሚሳተፉና ጎን ለጎንም የተግባርና የመስክ የልማት ስራ ጉብኝቶች እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን- የፖሊስ አባላት
Nov 19, 2025 63
ቦንጋ፤ ህዳር 10/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፖሊስ አመራርና አባላት ተናገሩ። በክልሉ "ከጂኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሃሳብ በየደረጃው ለሚገኙ የፖሊስ አመራርና አባላት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የፖሊስ አመራርና አባላትም የተሰጠው ስልጠና በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት ህዝብን ከማገልገል ባለፈ በሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የተሻለ ግንዛቤ ለመያዝ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል ኮማንደር እታለማው ተፈራ፣ ኢንስፔክተር አባይነህ አልዬ እና ምክትል ኢንስፔክተር አንድነት አበራ፤ የተሰጠው ስልጠና ወቅታዊ ሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮችን በመረዳት ለላቀ ህዝባዊ አገልግሎት የሚያዘጋጅ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህም ባለፈ ወቅታዊ ሁኔታዎችን በአግባቡ በመረዳት በዚሁ ልክ የፓሊስ አባላት አቅማችንን ማሳደግ ያለብን መሆኑን የተገነዘብንበት ነው ብለዋል። በሁሉም መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ከምንም በላይ የህዝብን ሰላም ማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተው ለዚህም የፖሊስ አባላት የላቀ ሃላፊነት ይጠበቅብናል ለዚህም ተዘጋጅተናል ሲሉ ተናግረዋል። የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን በማለትም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ የፖሊስ አባላት የህዝብና የሀገር ወገንተኝነታቸውን በተግባር በማሳየት ለሰላምና ለልማት ዘብ መቆም እንዳለባቸው ገልጸዋል። በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተመዘገበው ስኬት ውስጥ የፖሊስ ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተው በቀጣይም ይህንኑ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ ሀገር በመገንባት ሂደት በየሙያ መስኩ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አንስተው የፖሊስ አባላት የክልሉን ሰላምና ልማት በዘላቂነት ለማስቀጠል እንዲተጉ አሳስበዋል። የክልሉ መንግስት የፖሊስን አቅም በቴክኖሎጂ እና በስልጠና ጭምር ለማጠናከር የሚሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው ስልጠና ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተሞች የተወጣጡ የፖሊስ አባላትና አመራሮች ተሳትፈዋል።  
በክልሉ የአመራሩን አቅም በማጎልበት ልማታዊ እመርታዎችን የማስቀጠል ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Nov 19, 2025 56
ጋምቤላ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም በማጎልበት እየተመዘገቡ ያሉ ልማታዊ እመርታዎችን የማስቀጠል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ። ’’በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ’’ በሚል መሪ ሃሳበ በጋምቤላ ክልል ሁለተኛው ዙር የከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ ከሰዓት በኋላ በጋምቤላ ከተማ ተጀምሯል። በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሽኔ አስቲን በዚሁ ወቅት፤ እንደ ሀገር እተመዘገቡ የሚገኙ የልማት እመርታዎችን ማፋጠን ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በክልሉ የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችና ትሩፋቶችን ይበልጥ በማፍጠን የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የአመረሩን የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም የማጎልበቱ ተግባር ተጠናከሮ ይቀጥላል ብለዋል። በመደመር መንግሥት በግብርና፣ በገጠር ትራንስፎረሜሽን፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተሞች ልማት እና በሌሎችም ዘርፎች የታለመውን ሀገራዊ ለውጥ በተመሳሳይ ደረጃ ለመፈጸም የአመራሩን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት የመገንባቱ ሂደትም እንዲሁ። ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሕዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚቆይ ተመልክቷል።
ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ ነው
Nov 18, 2025 128
‎ሀዋሳ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በብልፅግና ፓርቲ የሥልጠና መድረክ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ። በአዳማ በተካሄደው የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሥልጠና ላይ የተሳተፉ የሲዳማ ክልል አመራሮች የጋራ የውይይት መድረክ ዛሬ ማምሻውን ተካሄዷል፡፡   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በፓርቲው የተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ በክልሉ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ፍጥነትንና ፈጠራን በማከል ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን የበጀት ዓመቱን የሥራ ዕቅድ በመከለስ ውይይት እየተደረገበት እንደሚገኝ ገልጸዋል።፡ በዚህም በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት፣ በግብርናና ገጠር ልማትና በሌሎች የትኩረት መስኮች የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ ተግባቦት መፍጠር እንደተቻለ ጠቁመዋል፡፡ ይህንን ገቢራዊ ለማድረግም በክልሉ ያሉ የሰላምና ጸጥታና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎችን በመጠቀም እንደሚሰራ ተናግረዋል።   ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠልም የጊዜ፣ የጉልበትና የበጀት ብክነትን በማስቀረት ባጠረ ጊዜ ውስጥ የተነደፉ ዕቅዶችን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም አስረድተዋል፡፡ ሰላምና ልማት ወዳዱን ህዝብ እንዲሁም ባለሀብቱን በማስተባበርም የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በተሻለ ሁኔታ እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል። ገቢን አሟጦ በመሰብሰብም የተሻለ የመፈፀም አቅም በመፍጠር ዕቅዶችን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወንም አቅጣጫ መቀመጡን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ይሰራሉ
Nov 18, 2025 172
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና አዘርባጃን የፓርላማ፣ የህዝብ ለህዝብና የኢንቨስትመንት ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ታገሰ ጫፎ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኤልቺን አሚርባዮቭን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።   በውይይታቸውም የሁለቱን አገራት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ህዝብ ለህዝብ ትስስር በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የሁለቱ ሀገራት ፓርላማዎች ትስስር የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ለማጠናከር አጋዥ መሆኑ ተገልጿል።   በዚሁ ወቅት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ እንዳሉት፤ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ለረጅም ዓመታት የዘለቀና እየተጠናከረ የመጣ ነው። ሁለቱ ሀገራት ሲቪል ሰርቪሱን ለማጠናከር እንዲሁም በትምህርት ዘርፍ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርጓትን ተግባራት እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቅሰው፤ የአዘርባጃን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሰማሩ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።   አፈ ጉባዔው አዘርባጃን ኮፕ 29ን ማስተናገዷን አንስተው ኢትዮጵያ የኮፕ 32ን በውጤታማነት እንድታስተናግድ አዘርባጃን ያላትን ልምድና ተሞክሮ እንድታጋራ ጠይቀዋል። የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኤልቺን አሚርባዮቭ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ያላቸውን ትስስር የበለጠ ለማጠናከር እንሰራለን ብለዋል።   አዘርባጃን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ለዓመታት የዘለቀ ግንኙነት፣ የህዝብ ለህዝብ፣ የባህልና የንግድ ትስስር ለማጠናከር እንደሚሰራ ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማስተናገድ በመመረጧ እንኳን ደስ ያላችሁ ያሉት አምባሳደር ኤልቺን፤ አዘርባጃን ኮፕ 32 በስኬት እንዲጠናቀቅ ሀገራቸው ያላትን ልምድና ተሞክሮ ለማጋራት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ
በመረጃ ላይ የተመሰረተና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት እየተሰጠ ነው
Nov 19, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ ላይ የተመሰረተና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት እየተሰጠ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዳንኤል ቴሬሳ ገለጹ፡፡ የውጭ ሀገራት በተለይም ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሥራ ስምሪት የሚያገኙ ሴቶችን ጤናና ደህንነት ጥበቃ በተመለከተ በተዘጋጀው "ኢኖቬት" የተሰኘ የአራት ዓመት ፕሮጀክት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዳንኤል ቴሬሳ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት የሚያገኙ ዜጎች በጥናትና መረጃ ላይ የተመሰረተ ዘላቂ መፍትሔ ማበጀት ያስችላል፡፡ በተለይም ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የሚሰማሩ ዜጎች ጤና ላይ ያተኮረ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው፤ የዜጎችን መብትና ደህንነት ማስጠበቅ ዋና ትኩረቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሪፎርሙ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪትን በመረጃ ላይ ወደ ተመሰረተ የአሰራር ስርዓት ለመቀየር ዲጂታል ቴክኖሎጂ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡   የኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት የሪፎርሙ አካል መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ የመረጃ ስርዓቱ ግልጽ፣ ቀልጣፋና ተጠያቂነት የሰፈነበትና አስተማማኝ የሥራ ዕድል የሚፈጥር የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መስጠት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡   ፕሮጀክቱ ወደ ሥራ የሚሰማሩ ዜጎች ተገቢ የሙያ ድጋፍ፣ ችግሮች ሲያጋጥሟቸው ፈጣን የቆንስላና የማህበራዊ አገልግሎት እንዲያገኙ ያግዛል ብለዋል፡፡   የ"ኢኖቬት" ፕሮጀክት አስተባባሪ ካሳሁን ሀብታሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሥራ ስምሪት የሚያገኙ ሴቶች ደህንነትና ጤና ማሻሻል ላይ በማተኮር ለውጤታማ ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   ዜጎች ወደ ውጭ ሀገራት ለሥራ ከመሰማራታቸው በፊት ስልጠና መስጠት፣ በተሰማሩበት ሀገራት ሆነው መረጃ እንዲያገኙ ማድረግ የእርስ መርስ መደጋገፍን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ የጽሁፍና የድምጽ መረጃዎች በተንቀሳቃሽ ስልኮች ተደራሽ እንዲሆኑ ይደረጋል ብለዋል። በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ የፕሮጀክቱ ተወካይ ሳምራዊት ሰለሞን (ዶ/ር) በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ሴቶች የስነ አዕምሮ፣ የስነ ተዋልዶና ሌሎች የጤና መረጃዎች ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በጀርመን ሀምቡርግ ዩንቨርሲቲ የኮፒውቲንግ እና ዳታ ሳይንስ ማእከል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ማርቲን ሴማን (ዶ/ር) የዜጎችን ደህንት ማስጠበቅ በተናጠል የሚሰራ አይደለም ብለዋል፡፡ "ኢኖቬት" የተሰኘው ፕሮጀክትም ቅንጅትን መሰረተ በማድረግ በቴክኖሎጂ በተደገፈ መንገድ መስራተ እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡  
በክልሉ ማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከልን በማጠናከር የሰላምና የልማት ስራዎች እንዲሳለጡ ይሰራል - ፖሊስ ኮሚሽን
Nov 19, 2025 62
ሆሳዕና፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከልን በማጠናከር የሰላምና የልማት ስራዎች እንዲሳለጡ በበለጠ ሀላፊነት እንደሚሰራ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን "ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሀሳብ ለፖሊስ አመራሮችና አባላት ለሶስት ቀናት በሆሳዕና ከተማ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ያሉ ፀጋዎችን በማልማት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰላምን በበለጠ ማስጠበቅና ዘላቂ ማድረግ ይገባል፡፡   ለዚህም ስኬት ማህበረሰቡን ያሳተፈ የወንጀል መከላከልን በበለጠ በማጠናከር የሰላምና የልማት ስራዎች እንዲሳለጡ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በዚህም የክልሉ ፖሊስ በታማኝነትና በቅንነት ማህበረሰቡን የማገልገል ሀላፊነቱን በበለጠ እንደሚወጣ አስታውቀዋል።   የምስራቅ ጉራጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ሙሰማ ጀማል በበኩላቸው የዞኑ ፖሊስ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመቀናጀት የአካባቢውን ሰላም የማስጠበቅና የተጀመሩ የልማት ስራዎች እንዳይስተጓጎሉ ባከናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። በዞኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናቅቀው የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ፖሊስ ሰላምና ደህንነት የማረጋገጥ ተግባር በበለጠ ሀላፊነት ይከናወናል ነው ያሉት፡፡   በክልሉ የሰላምና የልማት ስራዎች እንዲሳለጡ የተሰጣቸውን ሀላፊነት በበለጠ እንደሚወጡ የገለጹት ደግሞ ሳጅን ቤተል ሰጡ ናቸው፡፡ በስልጠናው የክልሉ ፖሊስ፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ፣ ወረዳና ከተማ ፖሊስ አመራሮችና አባላት ተሳትፈዋል፡፡ የስልጠናውን መጠናቀቅ ተከትሎም በሆሳእና ከተማ በመከናወን ላይ ያሉ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎች ጉብኝት ተካሂዷል።
የምገባ መርሐ ግብር ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ  ነው 
Nov 19, 2025 79
ጎንደር፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን የከተማዋ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ገለጹ። በጎንደር ከተማ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ቤቶች የምገባ መርሃ ግብር በከተማው አየር ጤና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ እንደገለጹት፤ በከተማው የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው።   ለስኬቱም የከተማ አስተዳደሩ 40 ሺህ ተማሪዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስፈልግን ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ባለሀብቶችና ተቋማትን በማሳተፍ በማሰባሰብ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል። የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት መምሪያ የስርዓተ ትምህርት ባለሙያ አቶ ሚዛኑ ነቅሎ በበኩላቸው፤ መርሃ ግብሩ በ44 ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልጸዋል። የምገባ መርሃ ግብሩ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉና የማቋረጥ ምጣኔን በመቀነስ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል። በትምህርት ዘመኑ ከ1 ሺህ በላይ የቅድመና አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የምገባ መርሀ ግብሩ ተጠቃሚ ይሆናሉ ያሉት ደግሞ የአየር ጤና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ሳሙኤል አታላይ ናቸው።   ህብረተሰቡ ለምገባ መርሃ ግብሩና ለትምህርት ቤቱ የግብዓት ማሟያ የሚውል ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን አስረድተዋል። ባለፈው ዓመት በትምህርት ቤቱ የተጀመረው የምገባ መርሃ ግብር በተማሪዎች የትምህርት ውጤት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ፤ ወላጆች፤ ተማሪዎችና የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደመረ አቅም ዜጎችን በማገዝ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Nov 19, 2025 66
ወላይታ ሶዶ ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡- የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደመረ አቅም ዜጎችን በማገዝና ሃብትን አቀናጅቶ በመምራት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡ በወላይታ ሶዶ ከተማ ክልል አቀፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ እና የ2018 ዓ.ም የበጋ ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በርካታ አቅመ ደካሞችንና አረጋዊያንን በማገዝ ብዙ መሰራቱን አስታውሰዋል። በተለይም የወጣቶች ወሰን የተሻገረ ነፃ አገልግሎት ሰዎችን ከማገዝም ባለፈ የጋራ ትርክትንና አብሮነትን የሚያጸና ተግባር መሆኑን አንስተው ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደመረ አቅም ዜጎችን በማገዝና ሃብትን አቀናጅቶ በመምራት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል።   በመሆኑም በክረምቱ የተከናወነውን በጎ ተግባር በመሰነቅ ለበጋውም በተሻለ ዝግጅት ዜጎችን ለማገልገል መዘጋጀት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የክልሉ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ካሰች ኤልያስ፤ በክልሉ ከ4 ነጥብ 5 ሚልዮን በላይ ወጣቶች የተሳተፉበት የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በማከናወን ከ8 ነጥብ 3 ሚልዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።   በመርሃ ግብሩ ከ15 ሺህ በላይ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታና ዕድሳት፣ 6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዩኒት ደም መሰብሰቡንና ሌሎችም ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። ይህ መልካም ተግባር በበጋውም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ኢኮኖሚ
የተረከብናቸው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርሶች ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው
Nov 19, 2025 42
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ ዛሬ ከጀርመናውያን ቤተሰቦች የተረከብናቸው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርሶች በተመሳሳይ በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ። በጀርመናውያን ቤተሰቦች እጅ የነበሩ 12 ልዩ ልዩ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቅርሶችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ተረክቧል፡፡   በርክክብ ስነ ስርዓቱ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙዔል ክፍሌ(ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ ፈርዲናንድ ቮን ወይሄ(ዶ/ር) ተገኝተዋል። የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ቅርሶች እኤአ 1921-1928 በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ልዩ መልዕክተኛ ለነበሩት ፈርቲዝ ዌይስ በንግስት ዘውዲቱ እና አጼ ኃይለሥላሴ በስጦታ ተበርክተው የነበሩ እና በግል የተገዙ ናቸው ብለዋል፡፡ አሁን ላይ በህይወት የሌሉት የፈርቲዝ ዌይስ የልጅ ልጅ ራሞርና ቤተሰቦቹ በራሳቸው ተነሳሽነት በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ በኩል ጥንታዊ ቅርሶቹን መልሰዋል ነው ያሉት፡፡ ቅርሶቹ ከቱሪዝም መስህብነታቸው ባሻገር ታሪክን ወደ ቤቱ የመለሱና የሀገራቱን ወዳጅነት በግልጽ ያሳየ መሆኑን ጠቁመው፤ ድርጊቱ በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኙ ቅርሶችን እንዲመልሱ የሚያበረታታ ነው ብለዋል።   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባበቂ ፕሬዚዳንት ሳሙዔል ክፍሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በስጦታ የተበረከቱም ሆነ የተወሰዱ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቅርሶችን እንዲመለሱ በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡   በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ ፈርዲናንድ ቮን ወይሄ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቅርሶቹ የተመለሱት ያለምንም ጣልቃ ገብነት በቅርሱ ባለቤት ቤተሰቦች መልካም ፈቃድ ነው ብለዋል፡፡ ይህም የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚያጠናክር ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡   ከተመለሱት ቅርሶች መካከል ጎራዴ፣ ዘውድ፣ አክሊል፣ ስዕሎችና ሌሎች የኢትዮጵያን ማንነት የሚገልጹ ቅርሶች እንደሚገኙበት የገለጹት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ዳይሬክተር ዮሃንስ አድገህ(ዶ/ር) ናቸው። ቅርሶቹ ከቱሪዝም መስህብነት ባሻገር ለጥናትና ምርምር ግብዓት ሆነው እንደሚያገለግሉም ተናግረዋል፡፡   በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ልዩ መልዕክተኛ የነበሩት ፍርቲዝ ዌይስ የልጅ ልጅ ፕሮፌሰር ራሞን ዌይስ በበኩላቸው፤ ቅርሶቹ ከግለሰብ ይልቅ ለኢትዮጵያ ይበልጥ ይጠቅማሉ ብለን እንደቤተሰብ መክረን መልሰናል ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያዩ
Nov 19, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ባለፈው ዓመት ወደ ማሌዥያ ኦፊሴላዊ ጉብኝት ካደረኩኝ አንድ ዓመት በኋላ፣ የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂምን በኢትዮጵያ ተቀብያለሁ ብለዋል።   ይህ የጉብኝት ልውውጥ ጥልቅ አጋርነታችንን የሚመሰክር ሲሆን ይህም በርካታ ቁልፍ ሰነዶችን በመፈረም ተጠናክሯል ነው ያሉት። የመግባቢያ ሰነዶቹ በቱሪዝም፣ በጤና፣ በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት፣ በኳላ ላምፑር ከተማ ምክር ቤት እና በአዲስ አበባ አስተዳደር የትብብር መስክ ላይ ያተኮሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል።   ባደረግነው የሁለትዮሽ ውይይት፣ ትብብራችንን የበለጠ ለማጠናከር እና ለማስፋት ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት አረጋግጠናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በመልዕክታቸው።
ኢትዮጵያ የተወሰዱባትን 12 ውድ ቅርሶች ተረከበች
Nov 19, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በ1920ዎቹ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ 12 ውድ ቅርሶችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት እና ምርምር ተቋም ተቀብሏል። ቅርሶቹ የፕሮፌሰር ራሞን አያት እንዲሁም በ1920ዎቹ በኢትዮጵያ የጀርመን ልዑክ በነበሩት ፍራንዝ ዊስ የአገልግሎት ዘመን ከኢትዮጵያ የተወሰዱ ሲሆን፣ ፍራንዝ እና ባለቤታቸው ሄድዊግ ገንዘብ ከፍለው የሰበሰቧቸው ናቸው። ለዩኒቨርሲቲው ከተበረከቱት ውድ ቅርሶች ውስጥ ዘውድ፣ ጋሻ፣ ጎራዴ፣ ዝናር፣ ስዕሎች እንዲሁም ከራስ ተፈሪ መኮንን የተበረከቱ ስጦታዎች ይገኙባቸዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ቅርሶቹ የኢትዮጵያ ሃብቶች ከመሆናቸው በተጨማሪ ለጥናትና ምርምር በግብዓትነት የሚያገለግሉ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በመላው ዓለም በግለሰቦች እጅ እና በተቋማት ውስጥ የሚገኙና የኢትዮጵያ ታሪክ አስረጂ የሆኑ ጥንታዊ ቅርሶች ወደ ሃገር እንዲመለሱ የማድረጉ ጥረትም ይቀጥላል ማለታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ችግር ፈቺ ፈጠራና መፍትሔዎችን እያስገኙ ነው
Nov 19, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ችግር ፈቺ ፈጠራና መፍትሔዎችን እያስገኙ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ፡፡ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንትን በማስመልከት የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መንግስት የኢንተርፕርነርሽፕ ስነ ምህዳሩን ምቹ ለማድረግ በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ ይገኛል። ባለፉት ሰባት ዓመታት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ ምህዳሩን ማስፋት የሚያስችሉ አሰራሮችና ተቋማት ሪፎርምና አጀንዳ ቀረፃ ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም መንግስት በመፍጠርና በመፍጠን አገልግሎቶችን በመስጠት ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡   የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከተቋቋመ ጀምሮ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ከግለሰብ እስከ ተቋማት ድረስ እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ኢንተርፕርነሮችን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ብቁና ንቁ ተወዳዳሪ በማድረግ ሀገራቸውን ከድህነት የሚያወጡ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ችግርን መሰረት ያደረጉ መፍትሄ ሰጪ ፈጠራዎችን እያስገኙ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ኢትዮጵያን የምንገነባበትና ወደ ፊት የምናስፈነጥርበት፤ ዓለም ከደረሰበት ደረጃ ለማድረስ የምንጠቀምበት መድረክ ነው ሲሉም ገልዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ያሳየ ነው 
Nov 18, 2025 99
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመፍጠርና መፍጠን የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ያሳየ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል፡፡   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤት በዚህ ሳምንት መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከእድሜው በላይ የሚጨበጥ ውጤት ማስመዝገብ የቻለ ተቋም ነው፡፡   የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመደመር መንግስት ላይ መፍጠር፣ መፍጠንና በዝላይ ማለፍ የሚሉ ጽንሰ ሀሳቦችን በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዓለም ከደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የግድ ሁሉንም ሂደት ማለፍ አይጠበቅም ያሉት ኃላፊው፤ ነባራዊውን ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ በዝላይ ማለፍ ይገባል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን የሚያስችላትን አቅም መገንባቷን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የታየው የመፍጠን፣ የመፍጠርና በዝላይ የማለፍ ውጤት የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በዓለም ላይ ያሉ ሥራዎችን ሁሉ ማከናወን የሚችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡   ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሁሉንም ሥራዎች በፍጥነት፣ በጥራትና በግልጸኝነት ማከናወን እንደሚችል ገልጸው፤ ፈጣን ዕድገት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በመዲናዋ ሁሉም ተቋማት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ነዋሪዎች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚያቀርቡትን ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አቅም መገንባቱን ነው የተናገሩት፡፡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የማያስፈልግበት ቦታ የለም ያሉት ምክትል ከንቲባው፤ የመዲናዋን ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥና ደህንነት ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው፤ የከተማ ሥራ በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ እና ውሳኔ የሚተላለፍበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡   ከዚህም ባለፈ መረጃዎችን ተንትኖ ለቀጣይ የልማት ዕቅዶች ለማዋል፤ እንዲሁም የከተማዋን የክትመት ሁኔታ ለመቆጣጠር ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የተከናወኑ አስደናቂ ሥራዎች መዲናዋን በበቂ የክትመት መረጃ ላይ ተመስርቶ ውሳኔ መስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ በመዲናዋ የሚከናወኑ ህገ ወጥ ግንባታዎችን፣ የመሰረተ ልማት እንቅስቃሴዎችንና ቀጣይ ለመስራት የታቀዱትን በመለየት በቂ መረጃ ይሰጣል ብለዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት በመስጠት የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡   ከተማ አስተዳደሩ ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመሩን ገልጸው፤ በቀጣይ በሌሎችም ዘርፎች በጋራ መስራት እንዳለብን አይተናል ብለዋል፡፡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ሥራዎችን ቀላል ፈጣንና ግልጽ ማድረግ እንደተቻለ በማንሳት፤ ከተማ አስተዳደሩ የጀመረውን የስማርት ሲቲ ግንባታ ለማላቅ በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በመዲናዋ ዘላቂና ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን በማጎልበት በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ ማከናወን ያስችላል ብለዋል፡፡
መገናኛ ብዙኃን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎችን ማጠናከር አለባቸው
Nov 18, 2025 112
አዲስ አበባ፤ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦መገናኛ ብዙኃን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎች ማጠናከር እንደሚኖርባችው የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ገለጸ። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የልማት ሥራዎች የነገዋን ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በሚያሳልጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንድትገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን የኢዜአ አመራር አባላት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) የሥራ ኃላፊዎችና የሙያተኞች ቡድን አባላትም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤት የቴክኖሎጂ ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።   የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ 'ኢንተለጀንስ ለሁሉም' በሚል መሪ ሃሳብ በሁሉም ዘርፍ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ተቋማትም የዕለት ከዕለት ሥራዎቻቸውን በቀላሉ የሚያከናውኑበት ምቹ የቴክኖሎጂ ምኅዳር እየተፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል። የበርካታ ዓለም ሀገራት የመገናኛ ብዙኃንና ሌሎች ተቋማት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ጥራትና ፍጥነት ያላቸውን ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።   መገናኛ ብዙኃን የኢትዮጵያ ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህል የሚያሳድጉበትን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የዘገባ ስራዎችን መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል። ይህም ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የፈጠራ መልካም አጋጣሚዎችን በመጠቀም የሙያተኞችን የሥራ ጫና የሚቀንሱበት ዕድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፤ በበኩላቸው በጉብኝቱ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ በአፍሪካ ከፍ ያለ ስራ ለመስራት ምን እያከናወነች እንዳለች መመልከታቸውን ተናግረዋል።   የኢንስቲትዩቱ ጉብኝታቸውም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሌሎች መስኮች የኢትዮጵያን የብልጽግና ርዕይ የሚያሳካ ምቹ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን እንደታዘቡም ገልጸዋል። በኢንስቲትዩቱም ታዳጊዎች የኢትዮጵያን መፃኢ እጣ ፋንታ በተሻለ ጉዞ ማጀብ የሚያስችል የፈጠራ ሥራ እያከናወኑ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባን ቴክኖሎጂ ብቻ የመጠቀም ባህል በመቀየር ለአህጉሪቷ ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀስ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ፈጠራ ስራዎች እያከናወነች እንደምትገኝ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።   በጉብኝቱ የተሳተፉ የኢዜአ አመራር አባላትም፤ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካዊያን ጭምር ትምህርት የሚሰጥ አመርቂ ስኬት ማስመዝገቧን እንደታዘቡ ገልጸዋል።   በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የፈጠራ ሙያተኛን ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራትም የነገዋን ኢትዮጵያ የተሻለ ማድረግ በሚያስችል የትልም ጉዞ ላይ መሆኗንም ተናግረዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኅዳር 07/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃን መርቀው ስራ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
የአፍሪካን ዘላቂ ብልጽግና ለማረጋገጥ ለክህሎትና ፈጠራ ከፍተኛ ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል
Nov 18, 2025 139
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦የአፍሪካን ዘላቂ ብልጽግና ለማረጋገጥ ምርታማነትን ማሳደግ፣ ለቴክኖሎጂ፣ ለክህሎትና ፈጠራ ከፍተኛ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የግሉ ዘርፍ ልማት፣ ቀጣናዊ ውህደት፣ ንግድ፣ የመሰረተ ልማት፣ ኢንዱስትሪ እና ቴክኖሎጂ ኮሚቴ አራተኛው ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል፡፡ መደበኛ ስብሰባው "ለዘላቂ እና አሳታፊ ዕድገት ቀጣናዊ ውህደትን ለማሳደግ የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን እና ፈጠራን መጠቀም" በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት ይካሄዳል፡፡ በውይይቱ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችና ፈጠራ የአፍሪካን ቀጣናዊ ትስስርና ዘላቂ ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡   የተመድ ምክትል ዋና ጸሐፊና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክላቨር ጋቴቴ ባደረጉት ንግግር፤ አፍሪካ በአህጉራዊ ውህደትና በፈጠራ ላይ በመመስረት ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን ወደ ዕድል መለወጥ ይገባታል ብለዋል፡፡ ዓለም በፈጣን የቴክኖሎጂ ዑደት፣ የጂኦ-ፖለቲካ ውጥረት እና የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶች ላይ እንደምትገኝ አንስተዋል፡፡ አፍሪካ በርካታ ታዳሽ ኃይሎች ያሏት መሆኑን የገለጹ ሲሆን በቅርቡ ተግባራዊ ያደረገችውን የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ጨምሮ ተወዳዳሪ የማይገኝላቸው ሃብቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ አፍሪካ ፈጠራን በመጠቀም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር እና መድኃኒት የሚያደርሱ ድሮኖችን በመስራት ለፈተናዎቿ ምላሽ መስጠት መጀመሯን በበጎ አንስተዋል፡፡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርታማነትን በዓመት እስከ 40 በመቶ ሊያሳድግ እንደሚችል ጠቅሰው፤ አፍሪካ ይህን ማስፋፋት ይጠበቅባታል ብለዋል፡፡   በአፍሪካ ለመሰረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ጠቁመው፤ ድንበር ተሻጋሪ የሆነ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአባል ሀገራትና ከአጋሮች ጋር በመተባበር የበለጸገች አፍሪካ ለመገንባት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል፡፡ የግሉ ዘርፍ ልማት፣ ቀጣናዊ ውህደት፣ ንግድ፣ የመሰረተ ልማት፣ ኢንዱስትሪ እና ቴክኖሎጂ ኮሚቴ ሊቀ-መንበር ማማድጃም ዲኒስ ድጃሎ በበኩላቸው፤ አፍሪካ ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ምርታማነትን ማሳደግ፣ በቴክኖሎጂ፣ በክህሎትና በፈጠራ ላይ ማተኮር አለባት ብለዋል፡፡   ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እሴትን የሚጨምሩና ተወዳዳሪነትን የሚያሳድጉ በመሆናቸው በስፋት መጠቀም እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለአፍሪካ ዘላቂ ዕድገትና ብልጽግና ምርታማነትን በፈጠራ ማሳደግ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ስፖርት
በሴካፋ ዞን ማጣሪያ ታንዛንያ 11 ግቦችን በማስቆጠር ጅቡቲን አሸነፈች
Nov 18, 2025 99
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት ጨዋታ ታንዛንያ ጅቡቲን 11 ለ 0 ረታለች። ማምሻውን በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሉክማን አሊ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። ኢሳ ቾሌ፣ ሳዳም ሃሚስ፣ ንሂንጎ ጁማ፣ ሶአን አዳም እና ዲስማስ አታናስ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።   ውጤቱን ተከትሎ ታንዛንያ በስድስት ነጥብ ምድብ ሁለትን እየመራች ነው። የታንዛንያው ሉክማን አሊ በስድስት ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ዩጋንዳ ሱዳንን 9 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች። ቡድኑ በስድስት ነጥብ በታንዛንያ በግብ ክፍያ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። የምድቡ ሶስተኛ ጨዋታዎች አርብ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄዱ ሲሆን ታንዛንያ ከዩጋንዳ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ጅቡቲ ከብሩንዲ ሌላኛው የምድቡ መርሃ ግብር ነው። በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዛሬ አራተኛ ቀኑን አስቆጥሯል።
በሴካፋ ዞን ማጣሪያ ዩጋንዳ ድል ሲቀናት ሶማሊያ እና ኬንያ አቻ ተለያዩ
Nov 18, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ዛሬ እየተደረጉ ይገኛል። በምድብ አንድ በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ዩጋንዳ ሱዳንን 9 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች። ኦውን ሙኪሳ እና ኤዜ ኮምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል።   ቶማስ ኦጌማ፣ ኦዊኖ ጆን በብሪያን፣ ኢስማኤል ፋሃድ፣ ባቢ አብዱልሻኩር እና አርንሎድ ካዬምባ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ዩጋንዳ በስድስት ነጥብ ምድቡን መምራት ጀምራለች። በአንጻሩ ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ሱዳን ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አምስተኛ ደረጃን ይዛለች። የዩጋንዳው ኦውን ሙኪሳ በውድድሩ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ወደ አራት ከፍ በማድረግ የኮከብ ግብ አስቆጣሪነቱን ተመሳሳይ ግቦች ካለው ኢትዮጵያዊው ዳዊት ካሳው ጋር በጋራ እየመሩ ነው። በተያያዘም በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተካሄደ የምድብ አንድ ጨዋታ ሶማሊያ እና ኬንያ አንድ አቻ ተለያይተዋል።   አናስ መሐመድ ለሶማሊያ፣ ራይስ ኦቺዬንግ ለኬንያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ አዘጋጇ ኢትዮጵያ ደቡብ ሱዳንን 4 ለ 1 በማሸነፍ በስድስት ነጥብ መሪነቷን አጠናክራለች። በምድብ ሁለት ታንዛንያ ከጅቡቲ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በአማራ ክልል የግሪሳ ወፍ በሰብል ላይ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተቻለ
Nov 19, 2025 63
ባሕርዳር/ ደሴ ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሶስት ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተው የግሪሳ ወፍ በሰብል ላይ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ‎በቢሮው የዕፅዋት ጥበቃ ባለሙያ አቶ አበበ አናጋው ፤ የግሪሳ ወፍ በክልሉ ሰሜን ሸዋ፣ ደቡብ ወሎና ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች መከሰቱን ለኢዜአ ተናግረዋል። ‎ቢሮው ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከጥቅምት 8/2018 እስከ ሕዳር 6/2018 ዓ.ም ድረስ ባደረገው በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት በሰብል ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን አስታውቀዋል።   ‎የኬሚካል ርጭቱ ‎ ግሪሳ ወፉ በሚያድርባቸው በተለዩ 604 ሄክታር የሚሸፍን ቦታዎች በተካሄደው ርጭት የግሪሳ ወፍ መንጋን ማስወገድ መቻሉን ገልጸዋል። ‎በርጭቱም 1 ሺህ 208 ሊትር ኬሚካል ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቁመው፤ በዚህም ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የለማ ሰብልን ከጉዳት መታደግ መቻሉን ባለሙያው አስረድተዋል። በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ደጀኔ ከበደ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ጅሌ ጥሙጋ እና ደዋጨፋ ወረዳዎች የግሪሳ ወፍ መንጋ ተከስቶ ነበር። የወፉን ማደሪያ ሥፍራ በመለየት ከ155 ሄክታር መሬት ላይ በተደረገ የአውሮፕላን ኬሚካል ርጭት በሰብል ላይ ጉዳት ሳይደርስ መከላከል መቻሉን ተናግረዋል።   በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ በበኩላቸው፤ በቃሉ ወረዳ የተከሰተውን የግሪሳ ወፍ በአውሮፕላን የታገዘ ኬሚካል ርጭት በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ተናግረዋል። አርሶ አደሩ የደረሰውን ሰብል በወቅቱ ፈጥኖ ከመሰብሰብ ባሻገር ተባይና የግሪሳ ወፍ ሲመለከት ፈጥኖ ለግብርና ባለሙያዎች መረጃ እንዲሰጥ መክረዋል።
አሳታፊ የደን አስተዳደር ስርዓት የተፈጥሮ ደኖችን ህልውና መጠበቅ አስችሏል
Nov 19, 2025 92
ሚዛን አማን፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ተግባራዊ የተደረገው አሳታፊ የደን አስተዳደር ስርአት የተፈጥሮ ደኖችን ህልውና መጠበቅ ያስቻለ መሆኑን የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ገለጸ። በኢትዮጵያ ሰፊ የደን ሽፋን ካላቸው አካባቢዎች መካከል የሚጠቀሰው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሁለት በባዮስፌር ሪዘርቭ የተመዘገቡ ጥብቅ የተፈጥሮ ደኖች መገኛ ነው። የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ለማ ገብረሚካኤል ለኢዜአ እንደገለጹት፤በክልሉ ከጥንት ጀምሮ ያለው የደን አጠባበቅ ባህል የደን ሃብቶችን መጠበቅ፣ ማልማትና መንከባከብ ያስቻለ እሴት ሆኖ ቀጥሏል።   በክልሉ ውስጥ ከሚገኘው አጠቃላይ የደን ይዞታ ውስጥ ከ760 ሺ ሔክታር በላይ የሚያካልሉ ሁለት ደኖች በባዮስፌር ጥብቅ የደን ስፍራነት በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት የተመዘገቡ መሆኑን ተናግረዋል። በካፋና ሸካ ዞኖች የሚገኙ ደኖችን ለመጠበቅ የተቋቋሙ ከ500 በላይ አሳታፊ የደን አስተዳደር ማኅበራት ለደኖቹ ሕልውና መጠበቅ የጎላ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን አንስተው በቀጣይም የደኖቹን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ለማሳደግና የኢኮቱሪዝም ቀጣና ለማድረግ የሚሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሠራዊት ቆጭቶ በበኩላቸው፤ አሳታፊ የደን አስተዳደር ጥበቃ ሥርዓት ከሸካቾ ብሔረሰብ ባህል ጋር የተሳሰረ የሃብት መጠበቂያ እሴት መሆኑን ገልጸዋል።   በመሆኑም በሥርአቱ ደን ከመጠበቅ ባሻገር ከዘርፉ ኢኮኖሚ በማመንጨት አካባቢውን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑበት መሆኑንም ተናግረዋል። በወረዳው የዮኪጭጪ ቀበሌ አሳታፊ ደን አስተዳደር ማህበር አባል አቶ ገብረሥላሴ ቶንዶሮ፤ ደንን መጠበቅ ከጥንት የወረስነው ባህል በመሆኑ የትኛውንም የደን ውጤት ያለ ፍቃድና ያለ አግባብ መቁረጥ አይቻልም ብለዋል።   ደኑ በደን ክልልነት ከተመዘገበ በኋላም በአሳታፊ ደን አስተዳደር ተደራጅተው ለደኑ ጥበቃ ከማድረግ ጎን ለጎን በውስጡ ማርን ጨምሮ ኮሮሪማ፣ ጥምዝና ሌሎች የደን ውጤቶችን በማምረት እየተጠቀሙ መሆኑን ተናግረዋል። የደን ሃብት ጥበቃ የቀደሙት ያወረሱን ሀብታችን በመሆኑ ጠብቆ ለትውልድ የማስተላለፍ ግዴታ አለብን ያለው ደግሞ የዩቲ ቀበሌ የአሳታፊ ደን አስተዳደር ማኅበር አባል ወጣት ተካልኝ ተሰማ ነው።   ተገቢ ባልሆነ መንገድ የሚቆረጥ ዛፍ እንዳይኖር በአሳታፊ የደን አስተዳደር በወጣው የጥበቃ መርሐ ግብር መሠረት ደኑን እየጠበቀ መሆኑን ገልጿል። የአሳታፊ ደን አስተዳደር ማኅበር የአንድ ቀበሌ ነዋሪና በደን አካባቢ ያሉ አባወራ የህብረተሰብ ክፍሎችን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን በደን ክልል ውስጥ ሕገ ወጥ ድርጊት እንዳይፈጸም በጥበቃ የሚከላከሉበት ሥርአት ነው። አሳታፊ የደን አስተዳደር ስርአት ዓላማውም የደን ሀብትን ዘላቂነት ማረጋገጥ፣ የብዝሃ ሕይወትን መጠበቅ፣ የካርበን ክምችትን መጨመር እንዲሁም በአካባቢው የሚኖሩ ማህበረሰቦችን ኑሮ ማሻሻል እና ከደን የሚገኘውን ጥቅም ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንዲያገኙ ማድረግ ነው።
ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን እየተንከባከብን ነው - አርሶ አደሮች
Nov 18, 2025 145
አምቦ፤ ህዳር 9/2018(ኢዜአ)፡- ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን እየተንከባከቡ መሆኑን የምዕራብ ሸዋ ዞን አርሶ አደሮች ተናገሩ። አርሶ አደሮቹ ከዚህ ቀደም በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በተተከሉ ችግኞች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እያገኙ መሆናቸውን ጠቁመው ዘንድሮም በችግኝ እንክብካቤው ላይ አተኩረዋል።   ከጨሊያ ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አስፋው ድንቁ ባለፉት ዓመታት በተከናወነ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተራቆተ እና የተጎዳ ማሳቸው አገግሞ አሁን ላይ በፊት ከሚያገኙት ምርት በእጥፍ እያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም የእርሻ ማሳቸው በጎርፍ ተጠርጎ ምርታማነቱ በመቀነሱ ስጋት ውስጥ ገብተው እንደነበረም አስታውሰዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በተከታታይ በተተከሉ ችግኞች የአፈር መሸርሸር በመቀነሱ የእርሻ ማሳቸው ምርታማነቱ መጨመሩን አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የጥራጥሬ ሰብሎችን እያለሙ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው የተተከሉ ችግኞች የመሬቱን ለምነት የሚጠብቁ በመሆኑ ለከብቶቻቸው መኖ ማግኘታቸውንና አካባቢያቸውም መልካም ገጽፅታ መላበሱን አውስተዋል።   ሌላው አርሶ አደር ፋይሳ ቀነኒ በበኩላቸው፣ በአካባቢያቸው የተጎዳ መሬት በአረንጓዴ ዐሻራ ልማት እንዲያገግም በመደረጉ ከዚህ ቀደም ከሚያለሙት የጥራጥሬ ሰብሎች በተጨማሪ ጥምር ጥቅም የሚሰጡ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን አንስተዋል፡፡ መርሃ ግብሩ ከመጀመሩ በፊት ዝናብ ወቅቱን ጠብቆ ስለማይዘንብ ብዙ መቸገራቸውን አስታውሰው አሁን ላይ ግን ዝናቡም ወቅቱን ጠብቆ በመዝነቡ ምርታማነታቸው ጨምሮ የተሻለ ገቢ እያገኙ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ በማስተባበር የእርከን ስራ ላይ የአፈር ለምነት እንዲጠብቅና የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ ለተከታታይ ዓመታት በሰሩት ስራ ለውጥ መመዝገቡን ተናግረዋል።   የጨሊያ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርናና መሬት አስተዳዳር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢነዑ ተሾመ በበኩላቸው፤ በወረዳው በሚከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ስራ የህብረተሰቡ ተሳትፎ እያደገ መጥቷል ብለዋል፡፡ በወረዳው በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለተተከሉት ችግኞች አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በወረዳው የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ከተጀመረ ወዲህ የአካባቢው ስነ ምህዳር ከመቀየሩም በላይ የአርሶ አደሮቹ ምርትና ምርታማነት መጨመሩን አመልክተዋል። በወረዳው በአረንጓዴ ዐሻራ ልማት መርሃ ግብር ከሃገር በቀል የዛፍ ችግኞች በተጨማሪ ለምግብነት የሚውሉ ማንጐ፣ ሙዝ፣ አቮካዶ እና ቡና ጭምር መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡
ሰውና ተፈጥሮ የተዋደዱበት ቆጠር ገድራ  ጥብቅ ደን
Nov 18, 2025 93
ሰውና ተፈጥሮ የተዋደዱበት ቆጠር ገድራ በጉራጌ ዞን ከሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል አንዱ ነው። ጥብቅ ደኑ ከጉራጌ ዞን ከወልቂጤ ከተማ በ42 ኪሎ ሜትር ርቀት በስተምሥራቅ በእዣ ወረዳ ቆጠር ገድራ ቀበሌ ይገኛል።   ጥብቅ ደኑ በበርካታ ሀገር በቀል ዛፎች የተሸፈነ፣ ሰውና ተፈጥሮ የተዋደዱበት፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ የህይወት እስትንፋስ ነው። የቆጠር ገድራ ጥብቅ ደን ቀልብን የሚስብ፣ ነፍስ በሀሴት የምትሞላበት፣ መንፈስ የሚታደስበት ውብ ስፍራ ነው። ቆጠር ገድራ ተዳፋታማ በሆነ ስፍራ የሚገኝ ሲሆን ብዛት ባላቸው ሀገር በቀል ዛፎች ማለትም ዝግባ፣ የኮሶ ዛፍ፣ የሀበሻ ፅድ የተሞላ ነው፡፡   የቆጠር ገድራ የተፈጥሮ ደን ለረጅም ዘመናት ከሰው ንክኪ ተጠብቆ የቆየው በአካባቢው ኅብረተሰብ ነባር ባህል መሠረት የጥንት አባቶች ደኑ እንዳይቆረጥ በቃል ኪዳን/ጉርዳ/ ስለተሳሰሩ መሆኑም ተገልጿል፡፡ 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተውጣጣ የጋዜጠኞች ቡድን በጉራጌ ዞን ከሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎች አንዱ የሆነውን የቆጠር ገድራ ጥብቅ ደንን ጎብኝቷል።   የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዘውዱ ዱላ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት ከጥንት ጀምሮ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ደን መቁረጥ እንደ ወንጀል የሚቆጠር፤ በአካባቢው ባህል የሚያስቀጣ ነውር ተግባር ነው፡፡ ጥብቅ ደኑ ከ350 ሄክታር መሬት በላይ እንደሚሸፍን እና በውስጡ ከ18 በላይ የዛፍ ዝርያዎች እንደሚገኙም አንስተዋል። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ መሰረት አመርጋ በበኩላቸው የጉራጌ ህዝብ በስራ ወዳድነቱና ታታሪነቱ የሚታወቅ ከተፈጥሮ ጋር ትልቅ ቁርኝት ያለው መሆኑን ተናግረዋል። በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የሚገኘው የቆጠር ገድራ ጥብቅ የተፈጥሮ ደን ከ700 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠረ የሚነገርለት ሲሆን ህብረተሰቡ ደኑን ጠብቆ ያቆየበት መንገድ ከተፈጥሮ ጋር ላለው ቁርኝት አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። ደኑን በዘላቂነት ጠብቆ በማቆየት አካባቢውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግናና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል።   ቆጠር ገድራ ጥብቅ ደን በውስጡ ከያዛቸው የዛፍ ዝርያዎች ባለፈ የበርካታ ብዝኃ ህይወት መኖሪያ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የእዣ ወረዳ ደን እና አካባቢ ጥበቃ ልማት ጽህፈት ቤት የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ሂደት አስተባባሪ ብርሃኑ ብርሼ ናቸው። እንደዚህ ዓይነት ጥብቅ ደኖች ሥነ ምሕዳርን በመጠበቅ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ችግሮችን ለመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ለሱዳን ግጭት ዓለም አቀፍ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል- ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Nov 19, 2025 145
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የሱዳን ግጭት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቀናጀ ምላሽ እንዲሰጥ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ያዘጋጀው ሁለተኛ የሱዳን የልዩ ልዑኮች ፎረም ዛሬ በጅቡቲ ተካሄዷል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ተዋንያን ተሳትፈዋል። ፎረሙ በሱዳን ላለው ቀውስ የተቀናጀ መልስ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።   የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የሱዳን ሰላም በሱዳናውያን የሚመራ፣ ቀጣናዊ ትብብር የተረጋገጠበት እና ዓለም በአንድ ድምጽ የሚደግፈው ሊሆን እንደሚገባ አመልክተዋል። በሱዳን ያለውን ግጭት ለማስቆም፣ ንጹሃን ዜጎችን ለመጠበቅ እና የኢጋድ ቀጣናን የተረጋጋ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን በሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ የሰብዓዊ እርዳታ መተላለፊያ እንዲከፈት እና ተአማኒነት ያለው የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። ኢጋድ ሱዳናውያን በሀገራቸው ሰላም እና ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ክብራቸው እንዲጠበቅ ያላቸው መሻት እንዲሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በመረጃው አመልክቷል።
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 497
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 637
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል።   ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል።   ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 526
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ሐተታዎች
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 136
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 317
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 389
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 558
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2104
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2348
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3233
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3324
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 1373
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 936
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6767
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5246
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 56587
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51899
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32602
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30116
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26312
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 24974
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24620
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24572
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 56587
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51899
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32602
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30116
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በጥምር ግብርና ስኬት ያስመዘገቡት አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ
Nov 14, 2025 258
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ - ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ጨዛ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ለዘመናት ባከናወኑት የግብርና ልማት ሥራ ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ የዘለለ አልነበረም። ዛሬ ላይ ሆነው ያን ዘመንና ያሳለፉትን ዕድሜ ሲያስታውሱ ይቆጫሉ። በኋላ ቀር መንገድ ሲያከናውኑት ከነበረው የግብርና ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆንም፤ ሀብት ማፍራትም ሳይችሉ ቀርተዋል።   አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ይባላሉ። ከሰበሰቡት ሰብል ጎተራቸው ሳይጎድል፣ ከእንስሳት እርባታ ስራቸውም ጥገታቸው ሳትነጥፍ ማየት የዘውትር ህልማቸው ነበር። ለም መሬት ይዘው ምርታማ ባለመሆናቸው ሲቸገሩ፣ የሚሰራ ጉልበት ይዘው ማዕዳቸው እየጎደለ የጎልማሳነት ዕድሜ መባቻ ድረስ ችግር ሲፈራረቅባቸው ዓመታትን አሳልፈዋል። ይህ ፍላጎታቸው ሰምሮ፣ ጓሯቸው ለምቶ፣ ቤታቸው ሞልቶና ጥሪት አፍርተው የማየት ውጥናቸው ሳይሳካ ዓመታት ቢቆጠሩም ዛሬ ግን በጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ነገሮች ተቀይረዋል። የዓመታት ምኞታቸውን ማሳካት ጀምረዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ለስኬት እንዲበቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢያቸው አርአያ የሆኑ አርሶ አደር አድርጓቸዋል። የጥምር ግብርና ስራቸው ለዓመታት ከነበሩበት ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ በማውጣት ለአፍም ለኪስም ሆኗቸዋል። የመንግስት የልማት ትኩረት የሆነው ጥምር ግብርና በውስን መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅንጅት እንዲያለሙ እድል ፍጥሮላቸዋል። በዋናነት በሰብል፣ በእንሰት፣ በፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ላይ አተኩረው እየሰሩ ይገኛሉ። ይህም የአንዱ ክፍተት በሌላው እየተሞለ ውጤታማ ስላደረጋቸው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው። ለቤት ፍጆታ ብቻ ያመርቱ የነበረው የእንሰት ምርትን በማስፋፋት ችግኙንና ተረፈ ምርቱን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጭምር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያመርቱት ገብስ ለሌሎች አርሶ አደሮች ምሳሌ መሆን ችለዋል።   ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ስለሚያረቡም ወተት ከማጀታቸው አይጠፋም። በጓሯቸው የሚያለሙትን አትክልትና ፍራፍሬ ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል። አርሶ አደሩ ከንብ ማነብ ሥራቸውም እንዲሁ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው። ከአካባቢው ስነምህዳር ምክንያት ብዙም ያልተለመደውን ቡና በመትከል ለፍሬ አብቅተዋል። የእሳቸውን ፈለግ የተከተሉ ሌሎች አርሶ አደሮችም ቡና ማልማት ጀምረዋል። በእጅ ያለን ሀብት ወደ ውጤት ለመቀየር ተግቶ መስራትና ጽናት ያስፈለጋል ያሉት አርሶ አደር ወልዴ፣ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ሙያዊ ድጋፍና የተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ለውጤታቸው ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የእርሻ ልማትና የእንስሳት እርባታውን በቅንጅት ማከናወናቸውም እንዲሁ። አርሶ አደር ወልዴ የዓመታት ቁጭታቸው ዛሬ መፍትሄ እያገኘ ነው። የጥምር ግብርና ሥራቸው በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉና ልጆቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል። መኖሪያ ቤትን ጨምሮ የተለያየ ሀብት ለማፍራት ምክንያት በመሆኑም ልማቱን አስፋፍቶ ለማከናወን አቅደዋል።   አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጭምር አርአያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙራዱ ብሩ ናቸው። ቀደም ሲል በገብስ ምርት ላይ ብቻ አተኩረው ይሰሩ የነበረውን የግብርና ሥራ እንዲቀይሩ ምክንያት እንደሆኗቸው ይገልጻሉ። ከአርሶ አደር ወልዴ በወሰዱት ልምድ ወደ ጥምር ግብርና ገብተዋል። በዚህም ድርቅ የመቋቋም አቅም ያለውን እንሰት በማሳቸው በስፋት ማልማት ጀምረዋል። የነበሯቸውን ሀገረሰብ የዳልጋ ከብቶች በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በመቀየር የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው እየሰሩ ነው። ጥምር ግብርና የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ከአርሶ አደር ወልዴ ተምሪያለሁ ይላሉ። ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባለፈ የመሬት ለምነትን ለማስጠበቅም ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ የጀመርነውን ሥራ እናጠናክራለን ሲሉም ነው የገለጹት።   የሙህር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ መኑር ጀማል በበኩላቸው "አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ በውስን መሬት ገብስ፣ እንሰት፣ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በጥምር በማልማት የራሳቸውን ህይወት ከመቀየር ባለፈ ለሌሎች አርሶ አደሮች አርአያ እየሆኑን ነው ብለዋል። አርሶ አደሩ በሽታ መቋቋም የሚችሉና ለመድሃኒትነት የሚፈለጉ የእንሰት ዝርያዎችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ በመጥፋት ላይ የነበሩ የእንሰት ዝርያዎችን የመታደግና የአፈር ለምነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የጥምር ግብርና አሰራር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ በመሆኑ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት። የአርሶ አደር ወልዴ ልምድን በማስፋት የሌሎች አርሶ አደሮችም ጓዳ ሞልቶ እንዲትረፈረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጥምር ግብርና አርሶ አደሩ ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ጭምር እንዲተርፍ የማድርጉ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል።   ልማቱ እርስ በእርስ የሚደጋገፉና በአንድ መሬት ላይ የተለያዩ ምርቶችን በማግኘት የተሻለ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚሰራው ሥራ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ በጥቂት መሬት ብዙ ማምረት መቻል ነው። በመሆኑም በተለይ የመሬት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በሥራ ውጤታማ ለመሆን ሁሉም ነገር ምቹና አልጋ በአልጋ መሆን የግድ እንዳልሆነ አርሶ አደሩ ጥሩ ማሳያ ናቸው። ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ዕድል እንዴት ወደሀብትነት መቀየር እችላለሁ ብለው ከሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ የእሳቸው የስኬት ጉዞ በቂ ማሳያ ነው። ሰርቶ ለመለወጥም ሆነ ሀብት ለማፍራት ችግሮችን በጽናት ማለፍ እና የሥራ ትጋት ወሳኝ ነውና ተሞክሯቸውን ማስፋት ያስፈልጋል።
  "ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ"
Nov 12, 2025 330
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ" ብርሃኑ ፍቃዱ -ከሰቆጣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ማብራራታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችበትን የ30 ዓመታት ታሪክ ለመቀልበስ ይህን ያህል ዓመት እንደማይወስድ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ተቋማዊ መሰረት የሌለው የሚያስቆጭ ብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል ስለመሆኑም አንስተዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ እና አቶ አድማሱ ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር የተወለዱበት ስፍራ፣ የኖሩበት ቀዬ፣ ያሳደጋቸው ማህበረሰብ ... የዘመናት ትዝታና ትውስታቸው እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህን የታሪካቸው አካል የሆነውን የባሕር በር ማጣትም የሁል ጊዜ ፀፀትና እንደ ሰውነት ጥላ አብሮዋቸው የሚዞር እውነታ ነው። ከአካባቢው ርቆ ለሚገኝ ሰው ትውስታውን ሲያወራ ለሌላው ተረት ተረት፤ ለራስ ደግሞ የውስጥ ቁስል ማገርሸት ሆኖ ነው የሚሰማው ይላሉ።   ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብንና የቀይ ባህር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሸፍጥ ማጣቷ በቀይ ባህር ላይ እየዋኙ፣ ውሃ እየተራጩ፣ በዳርቻው ነፋሻማ ስፍራ እየተዝናኑ... ለኖሩት ለእነ መለሰ እና አድማሱ መቼም የማይረሳ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ለአለም ማሕበረሰብ ጥያቄውን ሲያሳውቁ ተደብቆ ለቆየው ትውስታቸው አዲስ ተስፋ እንደሰጣቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለ12 ዓመታት እንዳገለገሉ በትውስታና ቁጭታቸውን ወደ ኋላ ተመልሰው ያወሳሉ። አሁን በሰቆጣ ከተማ የሚኖሩት አቶ መለሰ ይሄይስ ፤ የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ተደማሪ አቅም ነበር በወቅቱ ይላሉ።   ይህን የአሰብ ወደብንና የቀይ ባሕር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሴራ ኢትዮጵያ ስታጣ ይሰሩበት ከነበረው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ስራ አቁመው ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሰቆጣ መምጣታቸውን አውስተዋል። በራሳቸው ላይ ከደረሰባቸው የስራ እና ሃብትና ንብረት ማጣት ፣ እንግልትና ሌሎች ችግሮች በላይ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተነጠለችበትን ሁኔታ ሲያስቡና ሲያሰላስሉ እንደሚያስቆጫቸው ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን በማጣት የባሕር በር ብቻ ሳይሆን የገቢና ወጭ ንግድን፣ የነዳጅ ማጣሪያ ጭምር ነው ያጣችው ያሉት አቶ መለሰ፤ አሁን ጥያቄው መነሳቱ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ገናናነቷ ለመመለስ ያለመ አበረታች ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። መንግስት ያነሳው የባሕር በር ጥያቄም የዘመናት ቁጭታችንን፣ ብስጭታችንን እና ህልማችንን ከተደበቀ ትውስታ፤ ወደ አዲስ ተስፋ የወሰደ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ህጋዊና ታሪካዊ ነው ያሉት አቶ መለሰ ፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝም ለአዲሱ ትውልድ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።   ከ1973 ዓ.ም ጀምረው ለአስር ተከታታይ ዓመታት በአሰብ ወደብ የሲቪል መሃንዲስ ክፍል ሰራተኛ እንደነበሩ ያወሱት አቶ አድማሱ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባሕር ባር ባለቤት በሆነችባቸው ዘመናት ገናና እና የተከበረች ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል። የባሕር በሩ የኢትዮጵያ የገቢና ወጭ ንግድ የሚሳለጥበት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሄን ታላቅ ትሩፋትና ፀጋ ለማስመለስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ቁጭትና ትውስታችንን ወደ አዲስ ተስፋ የቀየረ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶችና ባንዳዎች እኩይ ሴራ የባሕር በር ካጣች ወዲህ ጥያቄውን ማንሳት የማይቻልበት የአፈናው ዘመን አክትሞ በለውጡ መንግስት መነሳቱ አበረታችና ለማስመለስም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ ስለባሕር ባር አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ለስኬታማነቱ የድርሻዬ እወጣለሁ ሲሉም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም