ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ የአፍሪካ የተስፋና የብልፅግና ተምሳሌት እየሆነች ነው
Jun 26, 2026 41
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በስንዴ ልማት፣ በከተማ ልማት እና ሌሎችም መስኮች የአፍሪካ የተስፋና የብልፅግና ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል።   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላትም ዛሬ ከአራዳ ክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን በአራት ኪሎ አካባቢ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ የማኖር ሥራ በኢትዮጵያ በተጨባጭ ትላልቅ ውጤቶችን እያስመዘገበ የሚገኝ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ባለፉት አምስት ዓመታት የምክር ቤቱ አባላት ከአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ችግኝ የተከሉበት ቦታ በአሁኑ ወቅት ለምልሞ «ጫካ» መሆን መቻሉን ጠቅሰው፥ ይህም መርሃ ግብሩ በተግባር ውጤት እያሳየ ለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል። ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ በዓለም ላይ የሰውን ልጅ እየፈተኑ ካሉ ጉዳዮች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ ዋነኛው መሆኑን የጠቀሱት ተጠሪ ሚኒስትሩ፥ ይህ የዓለም አየር ንብረት ለውጥ የመጣው በሰው ልጅ አላስፈላጊ የተፈጥሮ ጣልቃ ገብነት ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል።   ይህንን ችግር ለመቅረፍና ለመቀነስ በዓለም መድረኮች ላይ የተለያዩ ስምምነቶች፣ ውይይቶችና ኮንፈረንሶች እየተካሄዱ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ግን በተግባር የተለየ ታሪክ ለዓለም እየጻፈች ትገኛለች ብለዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት በተደረገው ከፍተኛ ሕዝባዊ ንቅናቄ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከልና ተንከባክቦ በማጽደቅ ለተለያዩ ዓላማዎች ማዋል መቻሉን ገልጸዋል። ዘንድሮ ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍልና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተደራጀ መልኩ የራሳቸውን ታሪካዊ ድርሻ ለማበርከት በንቅናቄው እየተሳተፉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ ሀገሪቱ በምግብ ራስን የመቻል ግብንና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የጀመረችውን ሥራ በከፍተኛ ሁኔታ እየደገፈ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም ከሰባት ዓመታት በፊት የተተከሉ ዘርፈ ብዙ ተክሎች ዛሬ ላይ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ከዚህም የተነሳ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕልና ሎሚ ያሉ የተለያዩ ምርቶች እንደየአካባቢው የግብርና ሥርዓተ ምህዳር ከፍተኛ ምርት እያስገኙ ነው ያሉት ተጠሪ ሚኒስትሩ አቮካዶ ከሀገር ፍጆታም ባለፈ ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑን አብራርተዋል። በሌላ በኩል አረንጓዴ ዐሻራ ባስገኘው ለውጥ የአበባ እፅዋቶች በመብዛታቸው በሀገሪቱ ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና የማር ምርት ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን አንስተዋል። በመርሃ ግብሩ ከተፈጥሮ መጎዳት ጋር ተያይዞ የመጣውን በረሃማነትና ድርቅን የመግታትና የመቆጣጠር ሥራ መሠራቱን ጠቁመዋል። የአፈር መሸርሸርን ማስቆም የተቻለ ሲሆን፣ የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር የውሃ ሀብት በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ የጠፉ ምንጮችና ሐይቆችም መልሰው እያገገሙ ይገኛሉ ብለዋል። ይህ የውሃ ሀብት ማደግ ደግሞ በሀገሪቱ የመስኖ ልማት ሥራ እንዲጨምር በማድረጉ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው ሥራ እጅግ ውጤታማ እንዲሆን አስችሏል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ፣ በከተማ ልማት እንዲሁም በስንዴ ልማትና በሌሎችም መስኮች ለአፍሪካውያን ጭምር አዲስ የተስፋና የብልጽግና ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን ገልጸዋል።   “ተስፋን እንትከል” የሚለው የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መሪ መልክትም የተቀረጸው ከዚህ በመነሳት መሆኑን ጠቅሰው፥ ተስፋ ያላት ሀገር፣ ተስፋ ያለው ሕዝብና ተስፋ ያለው ትውልድ እየተገነባ ነው ብለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለነገ የሚደረግ ትልቅ ኢንቨስትመንትና የነገ ተስፋ መሆኑን በመግለፅ፥ በአሁኑ ወቅት የችግኝ ተከላ ሥራ የሕዝብ የሥራ ባህልና ተቋማዊ አሠራር እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች በየቤታቸው፣ በየአካባቢያቸውና በየማሳቸው ጭምር ችግኝ ማፍላትና መትከል መደበኛ ሥራቸው መሆኑን በማንሳት። የምክር ቤት አባላት የጀመሩትን የችግኝ ተከላ ሥራ ክረምቱን ወደ መረጣቸው ማኅበረሰብ ሲመለሱ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ቀጣናዊ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች ነው
Jun 26, 2026 62
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ ወሳኝ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንትና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመ "ሂሊ ዲያሎግ-አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ ተካሂዷል።   የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ በመድረኩ፤ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ውጤታማ ስራ እያከናወነች ነው ብለዋል። በዚህም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በኤሌክትሪክ ኃይል፣ በመንገድና በመሳሰሉት መሰረተ ልማቶች በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጥ ገንቢ ሚና እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እስከ ታንዛኒያ ድረስ የኤሌክትሪክ መስመር በመዘርጋት የምትሰራው ውጤታማ የልማት ሥራም አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች መሆኗን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063ን ዕውን ለማድረግም አባል ሀገራት የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶችን መዘርጋት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊና ቀጣናዊ የመሰረተ ልማት ውጤቶችም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለዲጂታል ኢኮኖሚ የተሰጠው ትኩረትም ንግድና ኢንቨስትመንትን በማሳለጥ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች ጨምሮ ለውጭ አልሚዎች አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን አስረድተዋል። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የስትራቴጂክ ጥናትና ምርምር ማዕከል ኢኮኖሚስትና ተመራማሪ መሐመድ አል አባቢ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በሁሉም መስክ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ስትራቴጂክ አጋር ናት ብለዋል። በዚህም በምግብ ዋስትና፣ በታዳሽ ኃይልና ቁልፍ መሰረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ትብብር በመፍጠር እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ወሳኝ ድል ተቀዳጅቷል
Jun 26, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ አርባምንጭ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሰመረ ሀፍታይ በሰባተኛው ደቂቃ ግቧን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከሶሶት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ45 ነጥብ ደረጃውን ከ16ኛ ወደ 14ኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን ያስመዘገበው ወልዋሎ በሊጉ የመቆየት እድሉን ይበልጥ አስፍቷል። በአንጻሩ በሊጉ 16ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርባምንጭ ከተማ በ35 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። አርባምንጫ ከተማ ከሊጉ መውረዱ ይታወቃል። ዛሬ ቀን ላይ በተደረጉ የ37ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና መቀሌ 70 እንደርታን 3 ለ 0 አሸንፏል። ይህን ተከትሎም መቀሌ 70 እንደርታ ከአርባምንጭ ከተማ በመቀጠል ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረደ ሁለተኛ ቡድን ሆኗል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0፣ ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፈዋል።
በካፋ ዞን በዘንድሮ የመኸር እርሻ ከ126 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል
Jun 26, 2026 86
ቦንጋ ፤ ሰኔ 19 /2018 (ኢዜአ)፦ በካፋ ዞን በዘንድሮ የመኸር አዝመራ ከ126 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ። የዞኑ ግብርና መምሪያ የ2018 ዓመተ ምህረት የግብርና ተግባራት አፈጻጸም ግምገማና የ2018/19 የመኸር ግብርና ስራዎች ዕቅድ ንቅናቄ መድረክ አካሄዷል። በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ ለግብርናው ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረት በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።   ግብርና ሁሉን አቀፍ ለውጥ ለማስመዝገብ ወሳኝ ዘርፍ በመሆኑ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግና ዘመናዊ አሰራሮችን በመከተል ያለውን አቅም አስተባብሮ ወደ ስራ በመግባት የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል ብለዋል። በዘንድሮው የመኸር እርሻ 126 ሺህ 491 ሄክታር መሬት ለማልማት መታቀዱን ገልፀዋል። በዚህም የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በየደረጃው በቁርጠኝነት ይሰራል ያሉት አስተዳዳሪው፣ ለአረንጓዴ አሻራ፣ ለቡና ልማትና ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ልዩ ትኩረት ይሰጣል ነው ያሉት። የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ገረመው ገብሬ በበኩላቸው በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ3 ሚሊዮን 225 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።   ለዚህም የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን 40 በመቶ በማድረስና 30 በመቶ የሚሆነውን መሬት በክላስቴር በማልማት የታቀደውን ያህል ምርት ለማምረት ርብርብ ይደረጋል ብለዋል። የግብዓት እጥረት እንዳይገጥም የተፈጥሮ ማዳበሪያ አጠቃቀም ላይ ትኩረት እንደሚሰጥ ያነሱት አቶ ገረመው የማይታረስ መሬትን ዜሮ በማድረስ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በዘንድሮው የመኸር አዝመራ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ባለፈ ለኩታ ገጠም እርሻ ትኩረት በመስጠት ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚሰሩ የገለፁት ደግሞ የጠሎና ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አትርሴ ሸታቸው እና የሺሾ እንዴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደምሴ ገብረማርያም ናቸው። በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ123 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን በማልማት ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡንም ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።  
በከተማው በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በርካታ ወገኖችን ተጠቃሚ ሆነዋል
Jun 26, 2026 101
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፡-በወላይታ ሶዶ ከተማ በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በርካታ ወገኖችን ተጠቃሚ ለማድረግ መቻሉን የከተማዋ ከንቲባ እታገኝ ኃይለማርያም ገለጹ። በከተማው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ የ2018 ዓ.ም የበጋ ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ እና የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ እታገኝ ኃይለማርያም እንደገለጹት በከተማዋ በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በርካታ ወገኖችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።   በዘንድሮ ክርምትም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚከናወኑ ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት በማከናወን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ግብ ተጥሏል ነው ያሉት። ለክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተሰጠው ልዩ ትኩረት 219 የአቅመ ደካማ ቤቶች የሚገነቡና የሚታደሱ መሆናቸውንም አመልክተዋል። ከተማ አስተዳደሩ ለሥራው ውጤታማት መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትንና ግለሰቦችን በማቀናጀት እንደሚሰራም ጠቁመዋል። የተቸገሩ ወገኖችን ለመርዳትና በዘላቂነት ለማቋቋም በተለየ ትኩረት ይሰራል ያሉት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የከተማው ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ረዳት ፕሮፌሰር ዘገየ ጳውሎስ ናቸው።   በዘንድሮ ክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ 40 ሺህ 500 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ አመልክተዋል። የከተማው ወጣቶችና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ቡቃቶ በበኩላቸው በክረምት የበጎፍቃድ አገልግሎት ችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ፣ ቤት ግንባታና ዕድሳትን ጨምሮ በ18 ዘርፎች የበጎ ፈቃድ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። በተግባሩም 150 ሺህ የሚደርሱ የከተማው ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን ነው ያመለከቱት። በዛሬው እለት የቤታቸው ግንባታ ሥራ የተጀመረላቸው አቶ ማሞ ፋራንጆ እና ወይዘሮ አይናለም አሻ ከዚህ ቀደም ይኖሩበት የነበረው ቤት በመጎሳቆሉ ፀሐይና ዝናብ እየተፈራረቀባቸው ለችግር ሲጋለጡ ቆይተዋል። ዛሬ ቤታቸው በአዲስ መልክ ግንባታው በመጀመሩ መደሰታቸውን ጠቁመው፣ ድጋፍ ያደረጉላቸውን አካላት አመስግነዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።        
የሚታይ
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ የአፍሪካ የተስፋና የብልፅግና ተምሳሌት እየሆነች ነው
Jun 26, 2026 41
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በስንዴ ልማት፣ በከተማ ልማት እና ሌሎችም መስኮች የአፍሪካ የተስፋና የብልፅግና ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል።   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላትም ዛሬ ከአራዳ ክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን በአራት ኪሎ አካባቢ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ የማኖር ሥራ በኢትዮጵያ በተጨባጭ ትላልቅ ውጤቶችን እያስመዘገበ የሚገኝ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ባለፉት አምስት ዓመታት የምክር ቤቱ አባላት ከአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ችግኝ የተከሉበት ቦታ በአሁኑ ወቅት ለምልሞ «ጫካ» መሆን መቻሉን ጠቅሰው፥ ይህም መርሃ ግብሩ በተግባር ውጤት እያሳየ ለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል። ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ በዓለም ላይ የሰውን ልጅ እየፈተኑ ካሉ ጉዳዮች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ ዋነኛው መሆኑን የጠቀሱት ተጠሪ ሚኒስትሩ፥ ይህ የዓለም አየር ንብረት ለውጥ የመጣው በሰው ልጅ አላስፈላጊ የተፈጥሮ ጣልቃ ገብነት ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል።   ይህንን ችግር ለመቅረፍና ለመቀነስ በዓለም መድረኮች ላይ የተለያዩ ስምምነቶች፣ ውይይቶችና ኮንፈረንሶች እየተካሄዱ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ግን በተግባር የተለየ ታሪክ ለዓለም እየጻፈች ትገኛለች ብለዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት በተደረገው ከፍተኛ ሕዝባዊ ንቅናቄ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከልና ተንከባክቦ በማጽደቅ ለተለያዩ ዓላማዎች ማዋል መቻሉን ገልጸዋል። ዘንድሮ ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍልና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተደራጀ መልኩ የራሳቸውን ታሪካዊ ድርሻ ለማበርከት በንቅናቄው እየተሳተፉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ ሀገሪቱ በምግብ ራስን የመቻል ግብንና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የጀመረችውን ሥራ በከፍተኛ ሁኔታ እየደገፈ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም ከሰባት ዓመታት በፊት የተተከሉ ዘርፈ ብዙ ተክሎች ዛሬ ላይ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ከዚህም የተነሳ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕልና ሎሚ ያሉ የተለያዩ ምርቶች እንደየአካባቢው የግብርና ሥርዓተ ምህዳር ከፍተኛ ምርት እያስገኙ ነው ያሉት ተጠሪ ሚኒስትሩ አቮካዶ ከሀገር ፍጆታም ባለፈ ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑን አብራርተዋል። በሌላ በኩል አረንጓዴ ዐሻራ ባስገኘው ለውጥ የአበባ እፅዋቶች በመብዛታቸው በሀገሪቱ ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና የማር ምርት ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን አንስተዋል። በመርሃ ግብሩ ከተፈጥሮ መጎዳት ጋር ተያይዞ የመጣውን በረሃማነትና ድርቅን የመግታትና የመቆጣጠር ሥራ መሠራቱን ጠቁመዋል። የአፈር መሸርሸርን ማስቆም የተቻለ ሲሆን፣ የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር የውሃ ሀብት በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ የጠፉ ምንጮችና ሐይቆችም መልሰው እያገገሙ ይገኛሉ ብለዋል። ይህ የውሃ ሀብት ማደግ ደግሞ በሀገሪቱ የመስኖ ልማት ሥራ እንዲጨምር በማድረጉ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው ሥራ እጅግ ውጤታማ እንዲሆን አስችሏል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ፣ በከተማ ልማት እንዲሁም በስንዴ ልማትና በሌሎችም መስኮች ለአፍሪካውያን ጭምር አዲስ የተስፋና የብልጽግና ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን ገልጸዋል።   “ተስፋን እንትከል” የሚለው የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መሪ መልክትም የተቀረጸው ከዚህ በመነሳት መሆኑን ጠቅሰው፥ ተስፋ ያላት ሀገር፣ ተስፋ ያለው ሕዝብና ተስፋ ያለው ትውልድ እየተገነባ ነው ብለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለነገ የሚደረግ ትልቅ ኢንቨስትመንትና የነገ ተስፋ መሆኑን በመግለፅ፥ በአሁኑ ወቅት የችግኝ ተከላ ሥራ የሕዝብ የሥራ ባህልና ተቋማዊ አሠራር እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች በየቤታቸው፣ በየአካባቢያቸውና በየማሳቸው ጭምር ችግኝ ማፍላትና መትከል መደበኛ ሥራቸው መሆኑን በማንሳት። የምክር ቤት አባላት የጀመሩትን የችግኝ ተከላ ሥራ ክረምቱን ወደ መረጣቸው ማኅበረሰብ ሲመለሱ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ቀጣናዊ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች ነው
Jun 26, 2026 62
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ ወሳኝ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንትና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመ "ሂሊ ዲያሎግ-አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ ተካሂዷል።   የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ በመድረኩ፤ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ውጤታማ ስራ እያከናወነች ነው ብለዋል። በዚህም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በኤሌክትሪክ ኃይል፣ በመንገድና በመሳሰሉት መሰረተ ልማቶች በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጥ ገንቢ ሚና እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እስከ ታንዛኒያ ድረስ የኤሌክትሪክ መስመር በመዘርጋት የምትሰራው ውጤታማ የልማት ሥራም አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች መሆኗን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063ን ዕውን ለማድረግም አባል ሀገራት የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶችን መዘርጋት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊና ቀጣናዊ የመሰረተ ልማት ውጤቶችም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለዲጂታል ኢኮኖሚ የተሰጠው ትኩረትም ንግድና ኢንቨስትመንትን በማሳለጥ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች ጨምሮ ለውጭ አልሚዎች አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን አስረድተዋል። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የስትራቴጂክ ጥናትና ምርምር ማዕከል ኢኮኖሚስትና ተመራማሪ መሐመድ አል አባቢ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በሁሉም መስክ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ስትራቴጂክ አጋር ናት ብለዋል። በዚህም በምግብ ዋስትና፣ በታዳሽ ኃይልና ቁልፍ መሰረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ትብብር በመፍጠር እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
ፋይዳ የዲጂታል አገልግሎትን በማስፋት ፈጠራን ማዕከል ያደረጉ ዘመናዊ ተቋማትን መገንባት አስችሏል
Jun 26, 2026 146
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የዲጂታል አገልግሎትን በማስፋት ፈጠራን ማዕከል ያደረጉ ዘመናዊ ተቋማትን መፍጠር እያስቻለ መሆኑን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ የነዋሪዎችን የመታወቅ መብት ለማረጋገጥ፣ በአገልግሎት ሰጭና ተቀባዮች መካከል መተማመንን ለማዳበር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና የተሳለጠ አሰራር ለማንበር የዲጂታል መታወቂያ ገቢራዊ ተደርጓል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ በአዋጅ ቁጥር 1284/2015 ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቶ እስካሁን ከ46 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የግንኙነትና የባለድርሻ አካላት ዳይሬክተር ሳሚናስ ሰይፉ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በመላ ሀገሪቱ በ12 የምዝገባ ማሽኖች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እየተከናወነ ነው፡፡ ምዝገባው በኢትዮ ቴሌኮም፣ ኢትዮ-ፖስታ፣ በባንኮችና ለሌሎች አጋር ተቋማት የሚከናወን ሲሆን ተመዝጋቢዎች ፈጣን አገልግሎት የሚያገኙበት አሰራር ተዘርግቷል ብለዋል፡፡ በፕሮግራሙ በቀን ከሁለት ሚሊየን በላይ መረጃዎች እየተረጋገጡ ሲሆን እስካሁን የተረጋገጠላቸው ደንበኞች ቁጥር 104 ሚሊየን መድረሱን ገልጸዋል፡፡ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት የራስን ማንነት የመለያና ወደ ኢኮኖሚ የመግቢያ መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ማህበራዊ አገልግሎትን በቀላሉ ማግኘት ያስችላል ብለዋል፡፡ ፋይዳ ሚናው ማጭበርበርን ማስቀረት ብቻ አይደለም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ፈጠራና ዘመናዊነትን የተላበሱ ተቋማትን መፍጠር እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ በተቋማት መካከል መተማመን እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑን በማነሳት፤ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ጊዜና ቦታ መስጠቱን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ሀገር ለዜጎቿ ግልጽ ዕቅድ በማውጣት ተገቢውን በጀት ለመመደብ ተጨባጭ ማስረጃ ሆኖ ያገለግላልም ብለዋል፡፡ ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት ጋር የተሳሰሩ ተቋማት 150 መድረሳቸውን በማንሳት፤ የምዝገባ ሽፋኑን ወደ ሁሉም የገጠሪቱ አካባቢ ለማስፋት ተጨማሪ ግዙፍ ወኪሎችን ወደ ሥራ እንደሚገቡም ጠቁመዋል፡፡    
ኢትዮጵያ አዳዲስ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ስትራቴጂካዊ የትብብር ፖሊሲዎች የሚፈልቁባት ማዕከል ሆናለች
Jun 26, 2026 221
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም ያላት ዲፕሎማሲያዊ ሚና ትብብርን የሚያጠናክሩ አዳዲስ ፖሊሲዎች የሚፈልቁባት ስትራቴጂካዊ መድረኮች ማዕከል እንድትሆን ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ገለጹ። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንት እና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመው "ሂሊ ዳያሎግ - አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፣ በኢትዮጵያ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ እና የተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅና የአፍሪካ ሀገራት ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። የመድረኩ ዓላማ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶችና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር፣ በምጣኔ ሀብትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ የጋራ ዕድሎችን ለመፍጠር እንዲሁም ለአፍሪካ አመለካከቶችና ፍላጎቶች በዓለም አቀፍ መድረክ መሪ ሚና ለመጫወት ነው። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቀጣይነት ባለው ውይይት፣ በጋራ ምርምር እና በእውቀት ልውውጥ ላይ የተመሰረተ ዘላቂ ተቋማዊ አጋርነት መገንባት በአፍሪካና በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ትብብር ለማሳደግ አስፈላጊ ነው። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ በአፍሪካም ሆነ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና ግዙፍ አቅም የገነባች ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ ያስመዘገበችውን ከፍተኛ የኢኮኖሚ እድገት እና የኢንቨስትመንት አቅም መጠቀም ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ስልታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከደረሰችበት የቴክኖሎጂ እድገት፣ ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት እና ከወደብ ተደራሽነት መስፋፋት ጋር የተያያዙ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የበለጠ በጋራ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።   ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን እምቅ የትብብር አቅምና የኢንቨስትመንት አማራጮችን በጋራ ጥቅም ላይ ማዋል በሚችሉባቸው ስልታዊ ስምምነቶች ላይ ትኩረት አድርገው እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እያደገ የመጣው የዲፕሎማሲ የሀሳብ አመንጭነት እና ተፅዕኖ ፈጣሪነት በዓለም አቀፍ መድረክ ጎልቶ እየታየ መሆኑንም ገልጸዋል። ታዋቂው ኤምሬትስ የስትራቴጂክ ጥናትና ምርምር ማዕከል እውቅና ያለውን የሂሊ ዳያሎግ መድረክ በኢትዮጵያ ለማዘጋጀት የወሰነው ሀገሪቱ ያላትን ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖ፣ የማዕከልነት ሚና እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫነቷን ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑን ጠቁመዋል። አዲስ አበባ መድረኩን እንድታስተናገድ መመረጧ፣ ከተማዋ እያስመዘገበች ያለውን ዕድገትና ዓለም አቀፍ ጉባዔዎችን በማዘጋጀት ላለችው ስኬቶች እውቅና የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገሪቱ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና አዳዲስ የፖሊሲ ሀሳቦች የሚፈልቁባት እና ትልልቅ ዓለም አቀፍ ዓውደ-ጥናቶች የሚካሄዱባት ስትራቴጂካዊ ስፍራ ሆናለች ነው ያሉት።   በኢትዮጵያ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ በበኩላቸው፤ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት በረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንትና በጋራ ጥቅሞች ላይ ወደ ተመሰረተ ዘላቂ አጋርነት እየተሸጋገረ መሆኑን ገልጸዋል። በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ግንኙነት በተለይም በንግድ፣ በመሰረተ ልማት፣ በግብርና እና በንጹህ ኢነርጂ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል። ኤምሬቶች የአፍሪካን የንግድ እንቅስቃሴ ከቀጣናዊ እና ከዓለም አቀፍ ገበያዎች ጋር ይበልጥ ለማስተሳሰር የሚያስችሉ የተለያዩ ስትራቴጂካዊ የልማት ስራዎችን እያከናወነች መሆኗንም ተናግረዋል። ወደ ላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ የሚገኘው የኢትዮጵያና የኤምሬቶች ስትራቴጂካዊ አጋርነት ጠንካራ የኢኮኖሚ ትስስር እና ሰፊ ዕድልን የመጠቀም ትብብር ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ልዩ ስብሰባ የተለያዩ የብድርና ድጋፍ ስምምነት አዋጆችን አጸደቀ
Jun 26, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ልዩ ስብሰባ ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር ጋር የተፈረሙ ሶስት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነት አዋጆችን አጸደቀ፡፡ 6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ በዛሬው እለት ተካሂዷል።   ለምክር ቤቱ ከቀረቡት ስምምነቶች መካከል የመጀመሪያው ለዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ የእድገት ልማት ፖሊሲ ማስፈፀሚያ የሚውል የአራት መቶ ሰላሳ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ሺ (437,400,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ሁለተኛው የማህበረሰብ ተኮር የመሬት አያያዝ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል የአንድ መቶ አርባ አምስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ (145,500,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ሶስተኛው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመስኖ ልማት ለዘላቂ ምርታማነት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሀምሳ አራት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺ (54,600,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ምክር ቤቱም እነኚህን የብድርና ድጋፍ ስምምነት አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል።   የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ በዚሁ ወቅት፤ የብድርና ድጋፍ ስምምነቶች ኢትዮጵያ የምታከናውናቸው የልማት ተግባራት ምን ያክል ለውጥ እያመጡ እና የህብረተሰቡን ህይወት በተጨባጭ እየቀየሩ መሆናቸውን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ይበልጥ በማጠናከር፤ ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን በመጠንና በጥራት በማሳደግ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት አይነተኛ ሚና እንደሚኖራቸው ገልጸዋል። የወጣቶችን፣ ሴቶችን፣ የአርሶና አርብቶ አደሮችን ህይወት ለማሻሻል በሚደረገው ረብርብ ትልቅ የፋይናንስ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል። የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባትና የመስኖ ልማቶችን ለማዘመን እንደሚያግዝም እንዲሁ።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ኢትዮጵያ አዳዲስ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ስትራቴጂካዊ የትብብር ፖሊሲዎች የሚፈልቁባት ማዕከል ሆናለች
Jun 26, 2026 221
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም ያላት ዲፕሎማሲያዊ ሚና ትብብርን የሚያጠናክሩ አዳዲስ ፖሊሲዎች የሚፈልቁባት ስትራቴጂካዊ መድረኮች ማዕከል እንድትሆን ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ገለጹ። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንት እና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመው "ሂሊ ዳያሎግ - አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፣ በኢትዮጵያ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ እና የተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅና የአፍሪካ ሀገራት ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። የመድረኩ ዓላማ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶችና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር፣ በምጣኔ ሀብትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ የጋራ ዕድሎችን ለመፍጠር እንዲሁም ለአፍሪካ አመለካከቶችና ፍላጎቶች በዓለም አቀፍ መድረክ መሪ ሚና ለመጫወት ነው። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቀጣይነት ባለው ውይይት፣ በጋራ ምርምር እና በእውቀት ልውውጥ ላይ የተመሰረተ ዘላቂ ተቋማዊ አጋርነት መገንባት በአፍሪካና በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ትብብር ለማሳደግ አስፈላጊ ነው። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ በአፍሪካም ሆነ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና ግዙፍ አቅም የገነባች ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ ያስመዘገበችውን ከፍተኛ የኢኮኖሚ እድገት እና የኢንቨስትመንት አቅም መጠቀም ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ስልታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከደረሰችበት የቴክኖሎጂ እድገት፣ ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት እና ከወደብ ተደራሽነት መስፋፋት ጋር የተያያዙ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የበለጠ በጋራ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።   ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን እምቅ የትብብር አቅምና የኢንቨስትመንት አማራጮችን በጋራ ጥቅም ላይ ማዋል በሚችሉባቸው ስልታዊ ስምምነቶች ላይ ትኩረት አድርገው እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እያደገ የመጣው የዲፕሎማሲ የሀሳብ አመንጭነት እና ተፅዕኖ ፈጣሪነት በዓለም አቀፍ መድረክ ጎልቶ እየታየ መሆኑንም ገልጸዋል። ታዋቂው ኤምሬትስ የስትራቴጂክ ጥናትና ምርምር ማዕከል እውቅና ያለውን የሂሊ ዳያሎግ መድረክ በኢትዮጵያ ለማዘጋጀት የወሰነው ሀገሪቱ ያላትን ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖ፣ የማዕከልነት ሚና እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫነቷን ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑን ጠቁመዋል። አዲስ አበባ መድረኩን እንድታስተናገድ መመረጧ፣ ከተማዋ እያስመዘገበች ያለውን ዕድገትና ዓለም አቀፍ ጉባዔዎችን በማዘጋጀት ላለችው ስኬቶች እውቅና የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገሪቱ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና አዳዲስ የፖሊሲ ሀሳቦች የሚፈልቁባት እና ትልልቅ ዓለም አቀፍ ዓውደ-ጥናቶች የሚካሄዱባት ስትራቴጂካዊ ስፍራ ሆናለች ነው ያሉት።   በኢትዮጵያ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ በበኩላቸው፤ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት በረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንትና በጋራ ጥቅሞች ላይ ወደ ተመሰረተ ዘላቂ አጋርነት እየተሸጋገረ መሆኑን ገልጸዋል። በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ግንኙነት በተለይም በንግድ፣ በመሰረተ ልማት፣ በግብርና እና በንጹህ ኢነርጂ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል። ኤምሬቶች የአፍሪካን የንግድ እንቅስቃሴ ከቀጣናዊ እና ከዓለም አቀፍ ገበያዎች ጋር ይበልጥ ለማስተሳሰር የሚያስችሉ የተለያዩ ስትራቴጂካዊ የልማት ስራዎችን እያከናወነች መሆኗንም ተናግረዋል። ወደ ላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ የሚገኘው የኢትዮጵያና የኤምሬቶች ስትራቴጂካዊ አጋርነት ጠንካራ የኢኮኖሚ ትስስር እና ሰፊ ዕድልን የመጠቀም ትብብር ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ብልፅግና ፓርቲ አካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እውን እያደረገ ነው -ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)
Jun 26, 2026 220
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ አግላይ እሳቤዎችን በማስወገድ፣ በእኩልነት ላይ የተመሠረተ አካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እውን እያደረገ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የብልፅግና ፓርቲ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት መድረክ በጅግጅጋ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።   በዚሁ መድረክ ላይ የብልፅግና ፓርቲ የሱማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር መሐመድ ሻሌ፣ የሁሉም ክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ፓርቲው አግላይ እሳቤዎችን በማስወገድ፣ በእኩልነት ላይ የተመሠረተ አካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እውን እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ በማስመዝገብ በስኬት እየተራመደ መሆኑን ጠቁመዋል። የፓርቲውን እሳቤ ወደ ማኅበረሰቡ በማስረጽ ረገድ አሰባሳቢ ትርክትን ለመገንባት ያለመውን ይህንን መድረክ ላዘጋጁት የሱማሌ ክልል አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል። ለዘመናት ከመሀል ፖለቲካ ተገልሎና ከአገሪቷ ኢኮኖሚ ፍትሐዊ ተጠቃሚ ሳይሆን የኖረው የሱማሌ ሕዝብ በአሁኑ ወቅት በመሀል ፖለቲካና ኢኮኖሚ ላይ ያለው ተሳትፎ ከመቼውም ጊዜ በላይ ማደጉን ተናግረዋል።   ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በክልሉ የመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ትልቅ መነቃቃት መፈጠሩን ያነሱት ኃላፊው፤ የሱማሌ ክልል ሕዝብ ለዘመናት ሲናፍቃቸው የቆዩትን እንደ ጤና፣ መንገድና ትምህርት የመሳሰሉ መሠረታዊ የልማት አውታሮች በስፋትና በጥራት ተጠቃሚ መሆን መቻሉን አብራርተዋል። ይህ ለቀጣዮቹ ቀናት የሚቆየው የጅግጅጋው መድረክ፣ የክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በጥልቀት በመገምገም፣ በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርግ ታውቋል።
ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለዩት አጀንዳዎች የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ፍላጎት ያማከሉ ናችው - የሀገር ሽማግሌዎች
Jun 26, 2026 392
አዳማ፣ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ):- ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለዩት አጀንዳዎች የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ፍላጎት ያማከሉ መሆናቸውን የአዳማ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ሂደት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ባካተተ መልኩ ሲከናወን ቆይቶ በብሔራዊ ደረጃ የሚካሄድ ጉባኤ ላይ ደርሷል። የኮሚሽኑ አጀንዳ ማሰባሰብና የማደራጀት ተግባር በመጠናቀቁም ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል፤ ሐምሌ 08/2018 ዓ/ም በተለዩ ስምንት የመወያያ አጀንዳዎች ላይ ውይይት ይካሄዳል። በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተለዩት አጀንዳዎች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በግልጽ የመነጩ በመሆናቸው የሁሉንም ወገን ፍላጎት ያማከሉ ናቸው። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ፈይሳ መገርሳ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባዘጋጀው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ በንቃት መሳተፋቸውን አስታውሰዋል። በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ምሁራን፣ ሴቶች፣ መምህራን፣ ፖለቲከኞችና የሀገር ሽማግሌዎችን ጨምሮ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። የአንጀንዳ ማሳበሰብ ሂደቱ ላይ እንደመቆየታቸው ለብሔራዊ ጉባኤው የተለዩ አጀንዳዎች ወካይ እና ለችግሮቻችን መፍትሄ ለመሻት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። ሀገራዊ ጉባኤው እንዲሳካም የሚጠበቅባቸውን በመወጣቱ ረገድ እያከናወኑ ያሉትን ተግባር አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ጥላሁን ራጎ በበኩላቸው፣ በምክክር ሒደቱ ተሳትፈው በሕዝብ ውስጥ የሚነሱ ጥያቄዎችን ማንሳታቸውን አስታውሰዋል። ለብሔራዊ ጉባኤው የተለዩት አጀንዳዎች የሀገሪቱን ችግር ይፈታሉ የሚል ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸው "አጀንዳዎቹ አስፈላጊና ከሕዝቡ የመነጩ በመሆናቸው ትክክለኛና ተገቢ ናቸው፤ እኛም ለስኬቱ የበኩላችንን ድርሻ እናበረክታለን" ብለዋል። ለዚህም በተመረጡት አጀንዳዎች ላይ ተነጋግሮ በመግባባት ያሉ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በምክክሩ የተወከሉ አካላት ተወያይተው ያጸደቁትን ሐሳብ የመቀበል ግዴታ አለብን ሲሉም አስገንዝበዋል።    
የምክክር ኮሚሽኑ አጀንዳዎች ለሀገራዊ መግባባት መሰረት ይጥላሉ - የሀገር ሽማግሌዎች
Jun 26, 2026 383
ወልቂጤ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተለዩ አጀንዳዎች ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በመፍታት ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር ወሳኝ ሚና እንዳላቸው የጉራጌ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የጉራጌ የጆካ የሃገር ሽማግሌዎች ሰብሳቢ አጋዝ በለጠ ወልዴ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳዎችን ለመለየት የሄደበት ርቀት የሚደነቅ ነው፡፡ ኮሚሽኑ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ሲያከናውናቸው የነበሩ ተግባራት ህዝብን ያሳተፈ እንደነበር አስታውሰው፣ በየደረጃው ሲካሄዱ በነበሩ መድረኮች ህዝቡ ያሉትን አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ማቅረቡን አስታውሰዋል። የሃገር ሽማግሌዎችም በምክክር ሂደቱ በመሳተፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸው፣ በቀጣይም ለሀገራዊ መግባባት የሚሰሩ ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል። በኮሚሽኑ የቀረቡ አጀንዳዎችን ከራስ እና ከአካባቢያዊ ጥቅም በተሻገረ ሁኔታ በመመልከት ችግሮችን በሰከነ መንገድ በመምከር፣ በመወያየት በመግባባት ለሀገር ጥቅም መስራት ይገባል ብለዋል። አቶ ጠንክር ቢረጋ፤ በሐምሌ ወር ለሚካሄደው ዋናው ሐገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለዩት አጀንዳዎች ሳያግባቡ በቆዩ ጉዳዮች ላይ በግልጽ በመነጋገር ለልጆቻችን ታላቅ ሃገር ለማስተላለፍ ያስችለናል ብለዋል።   ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በአግባቡ በመጠቀም ለችግሮች በጋራ መፍትሔ ማበጀት ይገባል ነው ያሉት፡፡ የምክክርና የእርቅ ባህልን በማጠናከር በተለዩት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ መግባባት ላይ እንዲደረስ ለምክክሩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ የተናገሩት ሌላኛው የሃገር ሽማግሌ ደግሞ ሃይሌ ታቅንዳ ናቸው፡፡   ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በየአካባቢው በዜጎች የተነሱ አጃንዳዎችን አደራጅቶና ወስኖ ማቅረቡ በትኩረቶቹ ላይ ተነጋግሮ መግባባት ትልቅ አቅም መሆኑን ገልጸው፣ ለምክክሩ ስኬታማነት ተሳትፎዋቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እንዳስታወቀው የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል።
በአፍሪካና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድጉ ተግባራትን ማጠናከር ይገባል
Jun 26, 2026 463
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድጉ ተግባራትን ማጠናከር እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ገለጹ። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንት እና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመው "ሂሊ ዲያሎግ - አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፣ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ፣ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። የመድረኩም ዓላማ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶችና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር፣ በምጣኔ ሀብትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ የጋራ ዕድሎችን ለመፍጠር እንዲሁም ለአፍሪካ አመለካከቶችና ፍላጎቶች በዓለም አቀፍ መድረክ መሪ ሚና ለመጫወት ያለመ ነው። መድረኩ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ እና ስትራቴጂካዊ የጥናትና ምርምር ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በድሩ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ ቀጣይነት ባለው ውይይት፣ በጋራ ምርምር እና በእውቀት ልውውጥ ላይ የተመሰረተ ዘላቂ ተቋማዊ አጋርነት መገንባት በአፍሪካና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ትብብር ለማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለው ግንኙነት ዘርፈ ብዙ መሆኑን ጠቁመው፤ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ መስተጋብሮችን ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ በበኩላቸው፥ ሀገራቸው ከአፍሪካ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ ለማሳለጥ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። በወደብ ልማት፣ በኢነርጂ እና በሌሎችም ዘርፈ ብዙ መስኮች ከአፍሪካ ጋር በትብብር እየሰራች እንደምትገኝ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በእውቀት የሚመራ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ግንኙነትን ማጠናከር ይገባል
Jun 26, 2026 363
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ያላትን ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ግንኙነቶች በመረጃ ላይ በተመሰረተ ትንተና በመምራት ብሔራዊ ጥቅሟን ማስከበር የሚያስችሉ ተግባራትን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ አሁናዊ የኢትዮጵያ የብሔራዊ ደህንነት ተግዳሮቶችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች በሚል መሪ ሃሳብ ዓመታዊ የደህንነት የምክክር ጉባዔ በትናንትናው እለት ተካሂዷል።   በጉባዔው ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪ እና የተኩስ አመራር ኃላፊ ጀነራል አለምሸት ደግፌ፣ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ሀላፊ ጀነራል ይመር መኮንን፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ቀነአ ያደታ (ዶ/ር)፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ዘሪሁን አበበ ተገኝተዋል። በዚህ ወቅት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ ( ዶ/ር ) እንዳሉት፤ በሀገር ውስጥ ያለ የትኛውም ችግር ሀገረ መንግስቱን መገዳደር የሚችል አይደለም፡፡   ስለሆነም ውጫዊ በሆኑ ተግዳሮቶች ላይ ማተኮርና ከአካባቢው ሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት አስቀድሞ በመተንተን መምራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ግንኙነቶች በመረጃ ላይ በተመሰረተ ትንተና በመምራት ብሔራዊ ጥቅሟን ማስከበር የሚያስችላትን ተግባራት አጠናክራ ልትቀጥል እንደሚገባም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ዋና አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ በበኩላቸው፤ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚኖር ግንኙነት ገቢር ነበብ ስትራቴጂን መከተል እንደሚገባ አስረድተዋል።   የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ከተለያዩ ሀገራትና ዓለም አቀፍ የባህር ኃይል ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፤ ኢትዮጵያ ሰላም እንዳትሆን የሚፈልጉ የሀገር ውስጥና የውጭ ኃይሎችን ለመመከት የውስጥ ጥንካሬን ማጎልበት ያስፈልጋል ብለዋል።   ኢትዮጵያ የአካባቢውን ሀገራትና ሕዝቦችን በልማት በማስተሳሰር ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጠች መሆኗ ተፈላጊነቷን ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል። ብሔራዊ ጥቅምን ባስከበረ አካሄድ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያስተሳስሩ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት የተሻለ የጋራ ነገን መገንባት እንደሚገባ ተናግረዋል። የኤርትራ ሀገረ መንግስት ህልውና ከኢትዮጵያ መዳከም ጋር የተያያዘ መሆኑን የገለጹት አቶ ጌታቸው፤ የሀገሪቱ መሪ ለስልጣኑ ማቆያነት በኢትዮጵያ ትርምስ መፍጠርን ቋሚ አጀንዳ አድርጎ ቢይዝም የማይሳካ መሆኑን ገልጸዋል። የቀድሞ ህወሃት ጽንፈኛ ቡድንም ከስልጣን ውጪ መኖር የማይችል አመራር የያዘና የትግራይን ሕዝብ ሳይሆን የራሱን የስልጣን ጥም ለማርካት የሚተጋ መሆኑን አንስተዋል። የትግራይን ሕዝብ የልማት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ተስፋውን የሚያለመልሙ ተግባራትን ማጠናከር ይገባልም ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከፓኪስታን ጋር ያላትን አጋርነት ይበልጥ ለማሳደግ ትሰራለች-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jun 26, 2026 478
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከፓኪስታን ጋር ያላትን የሁለትዮሽ አጋርነት ለማጠናከር እንደምትሰራ አስታወቁ። የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሸሪፍ በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ላሸነፈውና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሚመራው ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሸሪፍ በሰጡት ምላሽ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ዘላቂ የወንድማማችነት መንፈስ የሚያንጸባርቅ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን በለውጥና በጽናት እየተጓዙ ያሉ ሀገራት መሆናቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለብልጽግና እና ለዕድገት ያላቸው ቁርጠኝነት ይበልጥ እንደሚያስተሳስራቸው አመልክተዋል። ሁለቱ ሀገራት በገቡት የጋራ ቃል ኪዳን መሠረት፣ በቀጣይ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እና አጋርነታቸውን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
ለምክክር የቀረቡ አጀንዳዎች ለቆዩ ሀገራዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ ናቸው
Jun 26, 2026 370
ቦንጋ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ለምክክር የቀረቡ አጀንዳዎች ለቆዩ ሀገራዊ ችግሮችና ለማያግባቡ ጉዳዮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከህዝብ የሰበሰባቸውን አጀንዳዎች ሲያደራጅ ቆይቶ በሐምሌ ወር ለሚጀምረው ዋናው የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ አድርጓል። የምክክር አጀንዳዎቹ ይፋ መደረጋቸውን ተከትሎ ኢዜአ በቦንጋ ከተማ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች አጀንዳዎቹ በጥልቅ እይታ ተደራጅተው የቀረቡ ሀገራዊ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም ለምክክር የተለዩት አጀንዳዎች ለቆዩ ችግሮችና ለአለመግባባቶች ምክንያት ሆነው የቆዩ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች እንደሆኑም ተናግረዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ብርሃኑ ገብሬ እና ወጣት አካሉ ወልደኢየሱስ፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ባለፉት ዓመታት ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ አጀንዳ በማሰባሰብና በመለየት ላደረገው ጥረት አድናቆታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ ከህዝብ የቀረቡ በርካታ አጀንዳዎችን አደራጅቶ ለምክክር ያቀረባቸው ስምንት አጀንዳዎች ሀገር መክራ መፍትሄ ልታመጣባቸው የሚገቡ አጀንዳዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በኮሚሽኑ ተለይተው ለምክክር የቀረቡ አጀንዳዎች ለቆዩ ሀገራዊ ችግሮችና ለአለመግባባት ምክንያት ለሆኑ ጉዳዮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ በጋራ መክሮ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ለሁሉም የምትመች ሀገር መገንባት ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል። የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት መምህር አገኘሁ ተፈሪ እና ወይዘሮ ፍሬሕይወት ገዛኸኝ፤ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ልማት እውን መሆን ከምክክር የተሻለ አማራጭ እንደሌለ አንስተው፣ በኮሚሽኑ ተለይተው በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ መክረን ችግሮቻችንን መፍታት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዋናው የምክክር ጉባኤ ለይቶ ያቀረባቸው የምክክር አጀንዳዎች የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌደራል ከተሞች ጉዳይ፣ የሐይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነት እና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስና እና መልካም አሥተዳደር እንዲሁም የሰላም ግንባታ መሆናቸው ይታወቃል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ አዳዲስ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ስትራቴጂካዊ የትብብር ፖሊሲዎች የሚፈልቁባት ማዕከል ሆናለች
Jun 26, 2026 221
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም ያላት ዲፕሎማሲያዊ ሚና ትብብርን የሚያጠናክሩ አዳዲስ ፖሊሲዎች የሚፈልቁባት ስትራቴጂካዊ መድረኮች ማዕከል እንድትሆን ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ገለጹ። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንት እና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመው "ሂሊ ዳያሎግ - አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፣ በኢትዮጵያ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ እና የተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅና የአፍሪካ ሀገራት ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። የመድረኩ ዓላማ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶችና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር፣ በምጣኔ ሀብትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ የጋራ ዕድሎችን ለመፍጠር እንዲሁም ለአፍሪካ አመለካከቶችና ፍላጎቶች በዓለም አቀፍ መድረክ መሪ ሚና ለመጫወት ነው። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቀጣይነት ባለው ውይይት፣ በጋራ ምርምር እና በእውቀት ልውውጥ ላይ የተመሰረተ ዘላቂ ተቋማዊ አጋርነት መገንባት በአፍሪካና በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ትብብር ለማሳደግ አስፈላጊ ነው። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ በአፍሪካም ሆነ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና ግዙፍ አቅም የገነባች ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ ያስመዘገበችውን ከፍተኛ የኢኮኖሚ እድገት እና የኢንቨስትመንት አቅም መጠቀም ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ስልታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከደረሰችበት የቴክኖሎጂ እድገት፣ ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት እና ከወደብ ተደራሽነት መስፋፋት ጋር የተያያዙ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የበለጠ በጋራ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።   ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን እምቅ የትብብር አቅምና የኢንቨስትመንት አማራጮችን በጋራ ጥቅም ላይ ማዋል በሚችሉባቸው ስልታዊ ስምምነቶች ላይ ትኩረት አድርገው እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እያደገ የመጣው የዲፕሎማሲ የሀሳብ አመንጭነት እና ተፅዕኖ ፈጣሪነት በዓለም አቀፍ መድረክ ጎልቶ እየታየ መሆኑንም ገልጸዋል። ታዋቂው ኤምሬትስ የስትራቴጂክ ጥናትና ምርምር ማዕከል እውቅና ያለውን የሂሊ ዳያሎግ መድረክ በኢትዮጵያ ለማዘጋጀት የወሰነው ሀገሪቱ ያላትን ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖ፣ የማዕከልነት ሚና እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫነቷን ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑን ጠቁመዋል። አዲስ አበባ መድረኩን እንድታስተናገድ መመረጧ፣ ከተማዋ እያስመዘገበች ያለውን ዕድገትና ዓለም አቀፍ ጉባዔዎችን በማዘጋጀት ላለችው ስኬቶች እውቅና የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገሪቱ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና አዳዲስ የፖሊሲ ሀሳቦች የሚፈልቁባት እና ትልልቅ ዓለም አቀፍ ዓውደ-ጥናቶች የሚካሄዱባት ስትራቴጂካዊ ስፍራ ሆናለች ነው ያሉት።   በኢትዮጵያ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ በበኩላቸው፤ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት በረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንትና በጋራ ጥቅሞች ላይ ወደ ተመሰረተ ዘላቂ አጋርነት እየተሸጋገረ መሆኑን ገልጸዋል። በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ግንኙነት በተለይም በንግድ፣ በመሰረተ ልማት፣ በግብርና እና በንጹህ ኢነርጂ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል። ኤምሬቶች የአፍሪካን የንግድ እንቅስቃሴ ከቀጣናዊ እና ከዓለም አቀፍ ገበያዎች ጋር ይበልጥ ለማስተሳሰር የሚያስችሉ የተለያዩ ስትራቴጂካዊ የልማት ስራዎችን እያከናወነች መሆኗንም ተናግረዋል። ወደ ላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ የሚገኘው የኢትዮጵያና የኤምሬቶች ስትራቴጂካዊ አጋርነት ጠንካራ የኢኮኖሚ ትስስር እና ሰፊ ዕድልን የመጠቀም ትብብር ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ብልፅግና ፓርቲ አካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እውን እያደረገ ነው -ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)
Jun 26, 2026 220
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ አግላይ እሳቤዎችን በማስወገድ፣ በእኩልነት ላይ የተመሠረተ አካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እውን እያደረገ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የብልፅግና ፓርቲ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት መድረክ በጅግጅጋ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።   በዚሁ መድረክ ላይ የብልፅግና ፓርቲ የሱማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር መሐመድ ሻሌ፣ የሁሉም ክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ፓርቲው አግላይ እሳቤዎችን በማስወገድ፣ በእኩልነት ላይ የተመሠረተ አካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እውን እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ በማስመዝገብ በስኬት እየተራመደ መሆኑን ጠቁመዋል። የፓርቲውን እሳቤ ወደ ማኅበረሰቡ በማስረጽ ረገድ አሰባሳቢ ትርክትን ለመገንባት ያለመውን ይህንን መድረክ ላዘጋጁት የሱማሌ ክልል አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል። ለዘመናት ከመሀል ፖለቲካ ተገልሎና ከአገሪቷ ኢኮኖሚ ፍትሐዊ ተጠቃሚ ሳይሆን የኖረው የሱማሌ ሕዝብ በአሁኑ ወቅት በመሀል ፖለቲካና ኢኮኖሚ ላይ ያለው ተሳትፎ ከመቼውም ጊዜ በላይ ማደጉን ተናግረዋል።   ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በክልሉ የመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ትልቅ መነቃቃት መፈጠሩን ያነሱት ኃላፊው፤ የሱማሌ ክልል ሕዝብ ለዘመናት ሲናፍቃቸው የቆዩትን እንደ ጤና፣ መንገድና ትምህርት የመሳሰሉ መሠረታዊ የልማት አውታሮች በስፋትና በጥራት ተጠቃሚ መሆን መቻሉን አብራርተዋል። ይህ ለቀጣዮቹ ቀናት የሚቆየው የጅግጅጋው መድረክ፣ የክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በጥልቀት በመገምገም፣ በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርግ ታውቋል።
ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለዩት አጀንዳዎች የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ፍላጎት ያማከሉ ናችው - የሀገር ሽማግሌዎች
Jun 26, 2026 392
አዳማ፣ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ):- ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለዩት አጀንዳዎች የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ፍላጎት ያማከሉ መሆናቸውን የአዳማ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ሂደት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ባካተተ መልኩ ሲከናወን ቆይቶ በብሔራዊ ደረጃ የሚካሄድ ጉባኤ ላይ ደርሷል። የኮሚሽኑ አጀንዳ ማሰባሰብና የማደራጀት ተግባር በመጠናቀቁም ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል፤ ሐምሌ 08/2018 ዓ/ም በተለዩ ስምንት የመወያያ አጀንዳዎች ላይ ውይይት ይካሄዳል። በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተለዩት አጀንዳዎች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በግልጽ የመነጩ በመሆናቸው የሁሉንም ወገን ፍላጎት ያማከሉ ናቸው። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ፈይሳ መገርሳ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባዘጋጀው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ በንቃት መሳተፋቸውን አስታውሰዋል። በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ምሁራን፣ ሴቶች፣ መምህራን፣ ፖለቲከኞችና የሀገር ሽማግሌዎችን ጨምሮ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። የአንጀንዳ ማሳበሰብ ሂደቱ ላይ እንደመቆየታቸው ለብሔራዊ ጉባኤው የተለዩ አጀንዳዎች ወካይ እና ለችግሮቻችን መፍትሄ ለመሻት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። ሀገራዊ ጉባኤው እንዲሳካም የሚጠበቅባቸውን በመወጣቱ ረገድ እያከናወኑ ያሉትን ተግባር አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ጥላሁን ራጎ በበኩላቸው፣ በምክክር ሒደቱ ተሳትፈው በሕዝብ ውስጥ የሚነሱ ጥያቄዎችን ማንሳታቸውን አስታውሰዋል። ለብሔራዊ ጉባኤው የተለዩት አጀንዳዎች የሀገሪቱን ችግር ይፈታሉ የሚል ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸው "አጀንዳዎቹ አስፈላጊና ከሕዝቡ የመነጩ በመሆናቸው ትክክለኛና ተገቢ ናቸው፤ እኛም ለስኬቱ የበኩላችንን ድርሻ እናበረክታለን" ብለዋል። ለዚህም በተመረጡት አጀንዳዎች ላይ ተነጋግሮ በመግባባት ያሉ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በምክክሩ የተወከሉ አካላት ተወያይተው ያጸደቁትን ሐሳብ የመቀበል ግዴታ አለብን ሲሉም አስገንዝበዋል።    
የምክክር ኮሚሽኑ አጀንዳዎች ለሀገራዊ መግባባት መሰረት ይጥላሉ - የሀገር ሽማግሌዎች
Jun 26, 2026 383
ወልቂጤ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተለዩ አጀንዳዎች ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በመፍታት ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር ወሳኝ ሚና እንዳላቸው የጉራጌ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የጉራጌ የጆካ የሃገር ሽማግሌዎች ሰብሳቢ አጋዝ በለጠ ወልዴ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳዎችን ለመለየት የሄደበት ርቀት የሚደነቅ ነው፡፡ ኮሚሽኑ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ሲያከናውናቸው የነበሩ ተግባራት ህዝብን ያሳተፈ እንደነበር አስታውሰው፣ በየደረጃው ሲካሄዱ በነበሩ መድረኮች ህዝቡ ያሉትን አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ማቅረቡን አስታውሰዋል። የሃገር ሽማግሌዎችም በምክክር ሂደቱ በመሳተፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸው፣ በቀጣይም ለሀገራዊ መግባባት የሚሰሩ ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል። በኮሚሽኑ የቀረቡ አጀንዳዎችን ከራስ እና ከአካባቢያዊ ጥቅም በተሻገረ ሁኔታ በመመልከት ችግሮችን በሰከነ መንገድ በመምከር፣ በመወያየት በመግባባት ለሀገር ጥቅም መስራት ይገባል ብለዋል። አቶ ጠንክር ቢረጋ፤ በሐምሌ ወር ለሚካሄደው ዋናው ሐገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለዩት አጀንዳዎች ሳያግባቡ በቆዩ ጉዳዮች ላይ በግልጽ በመነጋገር ለልጆቻችን ታላቅ ሃገር ለማስተላለፍ ያስችለናል ብለዋል።   ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በአግባቡ በመጠቀም ለችግሮች በጋራ መፍትሔ ማበጀት ይገባል ነው ያሉት፡፡ የምክክርና የእርቅ ባህልን በማጠናከር በተለዩት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ መግባባት ላይ እንዲደረስ ለምክክሩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ የተናገሩት ሌላኛው የሃገር ሽማግሌ ደግሞ ሃይሌ ታቅንዳ ናቸው፡፡   ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በየአካባቢው በዜጎች የተነሱ አጃንዳዎችን አደራጅቶና ወስኖ ማቅረቡ በትኩረቶቹ ላይ ተነጋግሮ መግባባት ትልቅ አቅም መሆኑን ገልጸው፣ ለምክክሩ ስኬታማነት ተሳትፎዋቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እንዳስታወቀው የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል።
በአፍሪካና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድጉ ተግባራትን ማጠናከር ይገባል
Jun 26, 2026 463
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድጉ ተግባራትን ማጠናከር እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ገለጹ። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንት እና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመው "ሂሊ ዲያሎግ - አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፣ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ፣ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። የመድረኩም ዓላማ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶችና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር፣ በምጣኔ ሀብትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ የጋራ ዕድሎችን ለመፍጠር እንዲሁም ለአፍሪካ አመለካከቶችና ፍላጎቶች በዓለም አቀፍ መድረክ መሪ ሚና ለመጫወት ያለመ ነው። መድረኩ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ እና ስትራቴጂካዊ የጥናትና ምርምር ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በድሩ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ ቀጣይነት ባለው ውይይት፣ በጋራ ምርምር እና በእውቀት ልውውጥ ላይ የተመሰረተ ዘላቂ ተቋማዊ አጋርነት መገንባት በአፍሪካና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ትብብር ለማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለው ግንኙነት ዘርፈ ብዙ መሆኑን ጠቁመው፤ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ መስተጋብሮችን ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ ረሺድ አብዱላ አልሼኺ በበኩላቸው፥ ሀገራቸው ከአፍሪካ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ ለማሳለጥ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። በወደብ ልማት፣ በኢነርጂ እና በሌሎችም ዘርፈ ብዙ መስኮች ከአፍሪካ ጋር በትብብር እየሰራች እንደምትገኝ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በእውቀት የሚመራ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ግንኙነትን ማጠናከር ይገባል
Jun 26, 2026 363
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ያላትን ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ግንኙነቶች በመረጃ ላይ በተመሰረተ ትንተና በመምራት ብሔራዊ ጥቅሟን ማስከበር የሚያስችሉ ተግባራትን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ አሁናዊ የኢትዮጵያ የብሔራዊ ደህንነት ተግዳሮቶችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች በሚል መሪ ሃሳብ ዓመታዊ የደህንነት የምክክር ጉባዔ በትናንትናው እለት ተካሂዷል።   በጉባዔው ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪ እና የተኩስ አመራር ኃላፊ ጀነራል አለምሸት ደግፌ፣ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ሀላፊ ጀነራል ይመር መኮንን፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ቀነአ ያደታ (ዶ/ር)፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ዘሪሁን አበበ ተገኝተዋል። በዚህ ወቅት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ ( ዶ/ር ) እንዳሉት፤ በሀገር ውስጥ ያለ የትኛውም ችግር ሀገረ መንግስቱን መገዳደር የሚችል አይደለም፡፡   ስለሆነም ውጫዊ በሆኑ ተግዳሮቶች ላይ ማተኮርና ከአካባቢው ሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት አስቀድሞ በመተንተን መምራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ግንኙነቶች በመረጃ ላይ በተመሰረተ ትንተና በመምራት ብሔራዊ ጥቅሟን ማስከበር የሚያስችላትን ተግባራት አጠናክራ ልትቀጥል እንደሚገባም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ዋና አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ በበኩላቸው፤ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚኖር ግንኙነት ገቢር ነበብ ስትራቴጂን መከተል እንደሚገባ አስረድተዋል።   የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ከተለያዩ ሀገራትና ዓለም አቀፍ የባህር ኃይል ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፤ ኢትዮጵያ ሰላም እንዳትሆን የሚፈልጉ የሀገር ውስጥና የውጭ ኃይሎችን ለመመከት የውስጥ ጥንካሬን ማጎልበት ያስፈልጋል ብለዋል።   ኢትዮጵያ የአካባቢውን ሀገራትና ሕዝቦችን በልማት በማስተሳሰር ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጠች መሆኗ ተፈላጊነቷን ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል። ብሔራዊ ጥቅምን ባስከበረ አካሄድ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያስተሳስሩ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት የተሻለ የጋራ ነገን መገንባት እንደሚገባ ተናግረዋል። የኤርትራ ሀገረ መንግስት ህልውና ከኢትዮጵያ መዳከም ጋር የተያያዘ መሆኑን የገለጹት አቶ ጌታቸው፤ የሀገሪቱ መሪ ለስልጣኑ ማቆያነት በኢትዮጵያ ትርምስ መፍጠርን ቋሚ አጀንዳ አድርጎ ቢይዝም የማይሳካ መሆኑን ገልጸዋል። የቀድሞ ህወሃት ጽንፈኛ ቡድንም ከስልጣን ውጪ መኖር የማይችል አመራር የያዘና የትግራይን ሕዝብ ሳይሆን የራሱን የስልጣን ጥም ለማርካት የሚተጋ መሆኑን አንስተዋል። የትግራይን ሕዝብ የልማት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ተስፋውን የሚያለመልሙ ተግባራትን ማጠናከር ይገባልም ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከፓኪስታን ጋር ያላትን አጋርነት ይበልጥ ለማሳደግ ትሰራለች-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jun 26, 2026 478
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከፓኪስታን ጋር ያላትን የሁለትዮሽ አጋርነት ለማጠናከር እንደምትሰራ አስታወቁ። የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሸሪፍ በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ላሸነፈውና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሚመራው ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሸሪፍ በሰጡት ምላሽ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ዘላቂ የወንድማማችነት መንፈስ የሚያንጸባርቅ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን በለውጥና በጽናት እየተጓዙ ያሉ ሀገራት መሆናቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለብልጽግና እና ለዕድገት ያላቸው ቁርጠኝነት ይበልጥ እንደሚያስተሳስራቸው አመልክተዋል። ሁለቱ ሀገራት በገቡት የጋራ ቃል ኪዳን መሠረት፣ በቀጣይ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እና አጋርነታቸውን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
ለምክክር የቀረቡ አጀንዳዎች ለቆዩ ሀገራዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ ናቸው
Jun 26, 2026 370
ቦንጋ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ለምክክር የቀረቡ አጀንዳዎች ለቆዩ ሀገራዊ ችግሮችና ለማያግባቡ ጉዳዮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከህዝብ የሰበሰባቸውን አጀንዳዎች ሲያደራጅ ቆይቶ በሐምሌ ወር ለሚጀምረው ዋናው የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ አድርጓል። የምክክር አጀንዳዎቹ ይፋ መደረጋቸውን ተከትሎ ኢዜአ በቦንጋ ከተማ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች አጀንዳዎቹ በጥልቅ እይታ ተደራጅተው የቀረቡ ሀገራዊ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም ለምክክር የተለዩት አጀንዳዎች ለቆዩ ችግሮችና ለአለመግባባቶች ምክንያት ሆነው የቆዩ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች እንደሆኑም ተናግረዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ብርሃኑ ገብሬ እና ወጣት አካሉ ወልደኢየሱስ፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ባለፉት ዓመታት ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ አጀንዳ በማሰባሰብና በመለየት ላደረገው ጥረት አድናቆታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ ከህዝብ የቀረቡ በርካታ አጀንዳዎችን አደራጅቶ ለምክክር ያቀረባቸው ስምንት አጀንዳዎች ሀገር መክራ መፍትሄ ልታመጣባቸው የሚገቡ አጀንዳዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በኮሚሽኑ ተለይተው ለምክክር የቀረቡ አጀንዳዎች ለቆዩ ሀገራዊ ችግሮችና ለአለመግባባት ምክንያት ለሆኑ ጉዳዮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ በጋራ መክሮ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ለሁሉም የምትመች ሀገር መገንባት ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል። የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት መምህር አገኘሁ ተፈሪ እና ወይዘሮ ፍሬሕይወት ገዛኸኝ፤ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ልማት እውን መሆን ከምክክር የተሻለ አማራጭ እንደሌለ አንስተው፣ በኮሚሽኑ ተለይተው በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ መክረን ችግሮቻችንን መፍታት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዋናው የምክክር ጉባኤ ለይቶ ያቀረባቸው የምክክር አጀንዳዎች የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌደራል ከተሞች ጉዳይ፣ የሐይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነት እና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስና እና መልካም አሥተዳደር እንዲሁም የሰላም ግንባታ መሆናቸው ይታወቃል።
ማህበራዊ
በከተማው በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በርካታ ወገኖችን ተጠቃሚ ሆነዋል
Jun 26, 2026 101
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፡-በወላይታ ሶዶ ከተማ በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በርካታ ወገኖችን ተጠቃሚ ለማድረግ መቻሉን የከተማዋ ከንቲባ እታገኝ ኃይለማርያም ገለጹ። በከተማው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ የ2018 ዓ.ም የበጋ ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ እና የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ እታገኝ ኃይለማርያም እንደገለጹት በከተማዋ በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በርካታ ወገኖችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።   በዘንድሮ ክርምትም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚከናወኑ ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት በማከናወን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ግብ ተጥሏል ነው ያሉት። ለክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተሰጠው ልዩ ትኩረት 219 የአቅመ ደካማ ቤቶች የሚገነቡና የሚታደሱ መሆናቸውንም አመልክተዋል። ከተማ አስተዳደሩ ለሥራው ውጤታማት መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትንና ግለሰቦችን በማቀናጀት እንደሚሰራም ጠቁመዋል። የተቸገሩ ወገኖችን ለመርዳትና በዘላቂነት ለማቋቋም በተለየ ትኩረት ይሰራል ያሉት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የከተማው ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ረዳት ፕሮፌሰር ዘገየ ጳውሎስ ናቸው።   በዘንድሮ ክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ 40 ሺህ 500 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ አመልክተዋል። የከተማው ወጣቶችና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ቡቃቶ በበኩላቸው በክረምት የበጎፍቃድ አገልግሎት ችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ፣ ቤት ግንባታና ዕድሳትን ጨምሮ በ18 ዘርፎች የበጎ ፈቃድ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። በተግባሩም 150 ሺህ የሚደርሱ የከተማው ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን ነው ያመለከቱት። በዛሬው እለት የቤታቸው ግንባታ ሥራ የተጀመረላቸው አቶ ማሞ ፋራንጆ እና ወይዘሮ አይናለም አሻ ከዚህ ቀደም ይኖሩበት የነበረው ቤት በመጎሳቆሉ ፀሐይና ዝናብ እየተፈራረቀባቸው ለችግር ሲጋለጡ ቆይተዋል። ዛሬ ቤታቸው በአዲስ መልክ ግንባታው በመጀመሩ መደሰታቸውን ጠቁመው፣ ድጋፍ ያደረጉላቸውን አካላት አመስግነዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።        
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በምርምር፣በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በማህበረሰብ አገልግሎት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው- አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር
Jun 26, 2026 98
ጂንካ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፡-ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ስራው ባለፈ በምርምር፣በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በማህበረሰብ አገልግሎት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ እና የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለተለያዩ አገልግሎቶች ያስገነባውን ዘመናዊ ህንፃ መርቀው ስራ አስጀምረዋል።   በዚሁ ሁነት ላይ ባደረጉት ንግግር ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ስራው ባለፈ በምርምር፣በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በማህበረሰብ አገልግሎት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰው የፕሮጀክቱ መመረቅም ለስራው ትልቅ እገዛ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በብቁ የሰው ሃይል እና በተደራጀ ግብአት እራሱን እያጠናከረ መሆኑን አንስተው በቀጣይም ለላቀ ስኬት መትጋት እንዳለበት ተናግረዋል።   የውስጥ ገቢ አቅሙን በማሳደግና ተቋማዊ አቅሙን በማጠናከር ራስ-ገዝ ለመሆን ጠንክሮ መስራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ከመማር ማስተማር ስራው ባሻገር ጠንካራ የምርምር ማእከል ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም አፅኖት ሰጥተዋል።   ለዩኒቨርሲቲው ስኬታማ ጉዞ የስራ አመራር ቦርዱ ድጋፍና እገዛውን በማጠናከር የሚቀጥል መሆኑንም አቶ አገኘሁ አረጋግጠዋል። የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዮሐንስ ይትባረክ (ዶ/ር )፤ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራት ማስጠበቅ፣ብቁ የሰው ሀይል ማፍራትና ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ የጥናትና ምርምር ስራዎችን የማበልፀግ ጥረት ይቀጥላል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው ተቋማዊ አቋሙን ለማጠናከር የካፒታል ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ስደተኞችን በማስተናገድ አፍሪካዊት ተምሳሌት ሀገር ናት -የጎረቤት ሀገራት ፍልሰተኞች
Jun 26, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ የምታሳየው የእንግዳ ተቀባይነት አያያዝ አፍሪካዊት ተምሳሌት ሀገር እንደሚያሰኛት የጎረቤት ሀገራት ፍልሰተኞች ተናገሩ። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎችን በመቀበል ተገቢውን መስተንግዶ እያደረገች ትገኛለች። በኢትዮጵያ ለሚገኙ ፍልሰተኞችም የዲጂታል መታወቂያ በማዘጋጀት ጭምር ከተቀባዩ ማህበሰረሰብ ጋር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር የሚያጠናክሩበት ምኅዳር ተፈጥሯል። በቅርቡም የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ስደተኞች በመጠለያ ጣቢያዎች ያላቸውን ሕይወት ከሀገሪቱ ብሔራዊ ሥርዓቶች ጋር ማስተሳሰርን ማዕከል ያደረገ የማካተት ፍኖተ ካርታ በይፋ አስጀምሯል። አስተያታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የጎረቤት ሀገራት ስደተኞች እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ስደተኞችን በእንግዳ ተቀባይነት ባህል ከመቀበል ባሻገር የልማት ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አስደናቂ ስራ እየሰራች ነው። ከኮንጎ የመጣው ወጣት ጆሴፍ ንዲኩሙኪዛ፤ ከአሥር ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ እየኖረ እንደሚገኝ ገልጿል።   የኢትዮጵያ የእንግዳ ተቀባይነት ባህልም ከተቀባዩ ማህበረሰብ ጋር ጭምር በሚያስተሳስር የልማት መርሃ ግብር ጭምር ተጠቃሚ የሚያደርግ አስደናቂ ተግባር የታጀበ መሆኑን ተናግሯል። የአህጉሪቷ አባል ሀገራትም ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ የምታሳየው የእንግዳ ተቀባይነት አያያዝ ትምህርት ሊወስዱበት የሚገባ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝቧል። ቡሩንዲያዊቷ ወጣት ሶሃንጌ ንዳይራጊሴ ማባንጋ በበኩሏ፤ ኢትዮጵያውያን ሰው አክባሪና በማንኛውም ሰዓትና ሁኔታ ድጋፍ የሚሰጡ ቀና ህዝቦች ናቸው ብላለች።   የኢትዮጵያ ህዝብና መንግሥት ለስደተኞች ምቹ ሁኔታ በመፍጠርና ዕድሎችን በማመቻቸት ከፍተኛ ድጋፍና እገዛ እያደረጉላቸው እንደሚገኝ አስረድታለች። ኢትዮጵያ እንደሀገሬ ተሰምቶኝ የምኖርባት ሁለተኛ ሀገሬ ናት ያለችው ደግሞ ኬንያዊቷ ወጣት ሃና ፓትሪክ ናት። የኢትዮጵያዊያን ደግነት ከሀገሯ ጉርብትና ጋር ተዳምሮ ደስተኛ ህይወት እንድትቀጥል ማስቻሉን ገልጻለች።  
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጠቀሜታ ከአገልግሎትም በላይ የሚሻገር ነው - አቶ ደስታ ሌዳሞ
Jun 26, 2026 161
በንሳ ዳዬ፤ ሰኔ19/2018(ኢዜአ) ፦ በየዓመቱ የሚከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለዜጎች የሚሰጠው ጥቅም ከአገልግሎትም በላይ እንደሆነ የሲዳማ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ በበጋ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተገነቡ መኖሪያ ቤቶችን ለአቅመ ደካሞች አስረክበዋል።   በዚህ ወቅትም ርዕሰ-መስተዳድሩ እንዳሉት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዜጎችን እለታዊና ዘላቂ ችግሮች ከመፍታት ባለፈ እርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህልን የሚያጎለብት የጋራ ማንነትንም የሚገነባ ነው።   በሲዳማ ክልል የተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎችን ማህበራዊ ችግሮች እየፈቱ መሆናቸውን አስረድተዋል። ተግባሩን ለማስቀጠልም ቅንጅታዊ ሥራዎች እንደሚጠናክሩ የገለጹት አቶ ደስታ፣ ዛሬ በዳዬ ከተማ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተገነባው ቤትም የዚሁ አካል መሆኑን አስረድተዋል።   ዛሬ የመኖሪያ ቤት ቁልፍ ከተረከቡ የበንሳ ዳዬ ከተማ አቅመ ደካሞች መካከል የ90 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋዋ ወይዘሮ ሙላቷ ይማም እንዳሉት ቤቱን በማግኘታቸው ዳግም የተወለዱ ያህል መደሰታቸውን ገልጸዋል። በዕድሜ መግፋት ምክንያት መስራት እንደማይችሉና የሚደግፋቸውም እንደሌለ ጠቅሰው ለተደረገላቸው ድጋፍ የክልሉን መንግስት አመስግነዋል። የተሰራላቸው መኖሪያ ቤት የተሟላ አገልግሎት የሚሰጥና ለሱቅ ጭምር የሚከራይ ክፍል የተዘጋጀለት በመሆኑ ቀጣይ ህይወታቸውን ለመምራት እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል። ከክልሉ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በበጋ ወራት በ13 ዘርፎች ከ654 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጉ የበጎ ፈቃድ ሥራዎች ተከናውነዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎሩ ከ354 ሺህ በላይ ወጣቶች የተሳተፉ ሲሆን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የተለያዩ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውም ታውቋል።
ኢኮኖሚ
ኢትዮጵያ ቀጣናዊ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች ነው
Jun 26, 2026 62
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ ወሳኝ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንትና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመ "ሂሊ ዲያሎግ-አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ ተካሂዷል።   የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ በመድረኩ፤ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ውጤታማ ስራ እያከናወነች ነው ብለዋል። በዚህም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በኤሌክትሪክ ኃይል፣ በመንገድና በመሳሰሉት መሰረተ ልማቶች በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጥ ገንቢ ሚና እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እስከ ታንዛኒያ ድረስ የኤሌክትሪክ መስመር በመዘርጋት የምትሰራው ውጤታማ የልማት ሥራም አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች መሆኗን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063ን ዕውን ለማድረግም አባል ሀገራት የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶችን መዘርጋት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊና ቀጣናዊ የመሰረተ ልማት ውጤቶችም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለዲጂታል ኢኮኖሚ የተሰጠው ትኩረትም ንግድና ኢንቨስትመንትን በማሳለጥ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች ጨምሮ ለውጭ አልሚዎች አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን አስረድተዋል። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የስትራቴጂክ ጥናትና ምርምር ማዕከል ኢኮኖሚስትና ተመራማሪ መሐመድ አል አባቢ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በሁሉም መስክ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ስትራቴጂክ አጋር ናት ብለዋል። በዚህም በምግብ ዋስትና፣ በታዳሽ ኃይልና ቁልፍ መሰረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ትብብር በመፍጠር እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
በካፋ ዞን በዘንድሮ የመኸር እርሻ ከ126 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል
Jun 26, 2026 86
ቦንጋ ፤ ሰኔ 19 /2018 (ኢዜአ)፦ በካፋ ዞን በዘንድሮ የመኸር አዝመራ ከ126 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ። የዞኑ ግብርና መምሪያ የ2018 ዓመተ ምህረት የግብርና ተግባራት አፈጻጸም ግምገማና የ2018/19 የመኸር ግብርና ስራዎች ዕቅድ ንቅናቄ መድረክ አካሄዷል። በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ ለግብርናው ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረት በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።   ግብርና ሁሉን አቀፍ ለውጥ ለማስመዝገብ ወሳኝ ዘርፍ በመሆኑ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግና ዘመናዊ አሰራሮችን በመከተል ያለውን አቅም አስተባብሮ ወደ ስራ በመግባት የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል ብለዋል። በዘንድሮው የመኸር እርሻ 126 ሺህ 491 ሄክታር መሬት ለማልማት መታቀዱን ገልፀዋል። በዚህም የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በየደረጃው በቁርጠኝነት ይሰራል ያሉት አስተዳዳሪው፣ ለአረንጓዴ አሻራ፣ ለቡና ልማትና ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ልዩ ትኩረት ይሰጣል ነው ያሉት። የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ገረመው ገብሬ በበኩላቸው በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ3 ሚሊዮን 225 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።   ለዚህም የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን 40 በመቶ በማድረስና 30 በመቶ የሚሆነውን መሬት በክላስቴር በማልማት የታቀደውን ያህል ምርት ለማምረት ርብርብ ይደረጋል ብለዋል። የግብዓት እጥረት እንዳይገጥም የተፈጥሮ ማዳበሪያ አጠቃቀም ላይ ትኩረት እንደሚሰጥ ያነሱት አቶ ገረመው የማይታረስ መሬትን ዜሮ በማድረስ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በዘንድሮው የመኸር አዝመራ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ባለፈ ለኩታ ገጠም እርሻ ትኩረት በመስጠት ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚሰሩ የገለፁት ደግሞ የጠሎና ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አትርሴ ሸታቸው እና የሺሾ እንዴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደምሴ ገብረማርያም ናቸው። በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ123 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን በማልማት ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡንም ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።  
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ልዩ ስብሰባ የተለያዩ የብድርና ድጋፍ ስምምነት አዋጆችን አጸደቀ
Jun 26, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ልዩ ስብሰባ ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር ጋር የተፈረሙ ሶስት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነት አዋጆችን አጸደቀ፡፡ 6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ በዛሬው እለት ተካሂዷል።   ለምክር ቤቱ ከቀረቡት ስምምነቶች መካከል የመጀመሪያው ለዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ የእድገት ልማት ፖሊሲ ማስፈፀሚያ የሚውል የአራት መቶ ሰላሳ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ሺ (437,400,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ሁለተኛው የማህበረሰብ ተኮር የመሬት አያያዝ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል የአንድ መቶ አርባ አምስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ (145,500,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ሶስተኛው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመስኖ ልማት ለዘላቂ ምርታማነት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሀምሳ አራት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺ (54,600,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ምክር ቤቱም እነኚህን የብድርና ድጋፍ ስምምነት አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል።   የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ በዚሁ ወቅት፤ የብድርና ድጋፍ ስምምነቶች ኢትዮጵያ የምታከናውናቸው የልማት ተግባራት ምን ያክል ለውጥ እያመጡ እና የህብረተሰቡን ህይወት በተጨባጭ እየቀየሩ መሆናቸውን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ይበልጥ በማጠናከር፤ ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን በመጠንና በጥራት በማሳደግ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት አይነተኛ ሚና እንደሚኖራቸው ገልጸዋል። የወጣቶችን፣ ሴቶችን፣ የአርሶና አርብቶ አደሮችን ህይወት ለማሻሻል በሚደረገው ረብርብ ትልቅ የፋይናንስ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል። የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባትና የመስኖ ልማቶችን ለማዘመን እንደሚያግዝም እንዲሁ።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት ግቦችን ከአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥማ እየተገበረች ነው
Jun 26, 2026 193
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት ግቦችን ከአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥማ እየተገበረች መሆኑ ተገለጸ፡፡ የመንገድ ደህንነት መድን ፈንድ አገልግሎት በመንገድ ትራፊክ አደጋ የሚደርሰውን ሞት ፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ለመቀነስ በዘርፉ የተቀመጡ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ግቦችን ለማሳካት የግማሽ ዘመን ስትራቴጂ አፈፃፀም ላይ ሀገር አቀፍ ጉባኤ እያካሄደ ይገኛል።   የኢትዮጵያ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አባሶ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ደህንነቱ የተጠበቀ የትራፊክ ፍሰት ለመፍጠር የተጀመሩ የስትራቴጂክ ስራዎች ተጨባጭ ፍሬ ማፍራት ጀምረዋል፡፡ አገልግሎቱ የትራፊክ አደጋ ስጋትን ለመቀነስ በቅንጅት ያከናወናቸው ተግባራት ተስፋ ሰጪ ውጤት እያስገኙ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ በተከናወኑት ስልታዊ የቅድመ-መከላከል ስራዎች ምክንያት የአደጋው ቁጥር ጉልህ መሻሻል እያሳየ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የወርልድ ሪሶርስ ኢንስቲትዩት (WRI) ከፍተኛ ባለሙያ ኢንጂነር ሰመረ ጅላሉ በበኩላቸው፤ ከ2021 እስከ 2030 የተቀመጡትን ዓለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት ግቦች ለማሳካት በርካታ ስኬታማ ተግባራት ማከናወኗን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት ግቦችን ከአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥማ እየተገበረች መሆኗን ገልጸዋል፡፡ በሕብረተሰቡ ዘንድ በትራፊክ አደጋ ተጋላጭነት ዙሪያ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ሲከናወኑ የቆዩ ሲሆን፣ በቀጣይም ተግባራቱ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በመድረኩ ተጠቅሷል፡፡ በዚሁ ሀገር አቀፍ ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት በዲጂታል የታገዘ የትራፊክ አደጋ መረጃ አስተዳደር ሥርዓት ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስረክቧል፡፡  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ፋይዳ የዲጂታል አገልግሎትን በማስፋት ፈጠራን ማዕከል ያደረጉ ዘመናዊ ተቋማትን መገንባት አስችሏል
Jun 26, 2026 146
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የዲጂታል አገልግሎትን በማስፋት ፈጠራን ማዕከል ያደረጉ ዘመናዊ ተቋማትን መፍጠር እያስቻለ መሆኑን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ የነዋሪዎችን የመታወቅ መብት ለማረጋገጥ፣ በአገልግሎት ሰጭና ተቀባዮች መካከል መተማመንን ለማዳበር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና የተሳለጠ አሰራር ለማንበር የዲጂታል መታወቂያ ገቢራዊ ተደርጓል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ በአዋጅ ቁጥር 1284/2015 ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቶ እስካሁን ከ46 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የግንኙነትና የባለድርሻ አካላት ዳይሬክተር ሳሚናስ ሰይፉ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በመላ ሀገሪቱ በ12 የምዝገባ ማሽኖች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እየተከናወነ ነው፡፡ ምዝገባው በኢትዮ ቴሌኮም፣ ኢትዮ-ፖስታ፣ በባንኮችና ለሌሎች አጋር ተቋማት የሚከናወን ሲሆን ተመዝጋቢዎች ፈጣን አገልግሎት የሚያገኙበት አሰራር ተዘርግቷል ብለዋል፡፡ በፕሮግራሙ በቀን ከሁለት ሚሊየን በላይ መረጃዎች እየተረጋገጡ ሲሆን እስካሁን የተረጋገጠላቸው ደንበኞች ቁጥር 104 ሚሊየን መድረሱን ገልጸዋል፡፡ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት የራስን ማንነት የመለያና ወደ ኢኮኖሚ የመግቢያ መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ማህበራዊ አገልግሎትን በቀላሉ ማግኘት ያስችላል ብለዋል፡፡ ፋይዳ ሚናው ማጭበርበርን ማስቀረት ብቻ አይደለም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ፈጠራና ዘመናዊነትን የተላበሱ ተቋማትን መፍጠር እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ በተቋማት መካከል መተማመን እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑን በማነሳት፤ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ጊዜና ቦታ መስጠቱን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ሀገር ለዜጎቿ ግልጽ ዕቅድ በማውጣት ተገቢውን በጀት ለመመደብ ተጨባጭ ማስረጃ ሆኖ ያገለግላልም ብለዋል፡፡ ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት ጋር የተሳሰሩ ተቋማት 150 መድረሳቸውን በማንሳት፤ የምዝገባ ሽፋኑን ወደ ሁሉም የገጠሪቱ አካባቢ ለማስፋት ተጨማሪ ግዙፍ ወኪሎችን ወደ ሥራ እንደሚገቡም ጠቁመዋል፡፡    
ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ሥጋትን መከላከልና ሊከሰቱ ለሚችሉ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ ትልቅ ተቋም ገንብታለች - ኢጋድ
Jun 26, 2026 254
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ሥጋትን መከላከልና ሊከሰቱ ለሚችሉ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችል ትልቅ ተቋም መገንባቷን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን /ኢጋድ/ ገለጸ፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢጋድ ቀጣናዊ የሳይበር የተግባር ልምምድ ስልጠና በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡   በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና የጅቡቲ ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኢጋድ ተጠሪ አበባው ቢሆነኝ እንዳሉት፤ የሳይበር ደህንነት ስጋት በአንድ ሀገር ብቻ የተገደበ ሳይሆን ድንበር ተሻጋሪ ዓለም አቀፍ ሥጋት ነው፡፡ ዓለም በደረሰበት የዲጂታል አብዮት ዘመን የሳይበር ደህንነት ሥጋት ዓለም አቀፍ የጋራ ሥጋት እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የኢጋድ አባል ሀገራት በመተባበርና ተቋማዊ አሰራራቸውን በማጠናከር ቁልፍ መሠረተ ልማቶቻቸውን በጋራ መጠበቅ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የሳይበር ደህንነት አደጋን መከላከል የሚቻለውም በጋራ ነው ያሉት ተጠሪው፤ የኢጋድ አባል ሀገራት ድንበር ተሻጋሪ የሳይበር ደህንነት ስጋትን መከላከልና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል ትብብር መፍጠር እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ከቀጣናው ሀገራት ሁሉ የተደራጀና ጠንካራ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ ኢጋድ ያዘጋጀው የተግባር ስልጠናም በሀገራት መካከል ልምድ መለዋወጥ ያስችላል ብለዋል፡፡ ኢጋድ አባል ሀገራቱ የሳይበር ደህንነት ሥጋትን ለመከላከልና አደጋ ሲደርስ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችሉበትን የአቅም ግንባታ ስልጠና አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡   የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ፤ የሀገሪቱን ቁልፍ የመሠረተ ልማቶች የመጠበቅ ኃላፊነቱን በብቃት መወጣት የሚያስችል ተቋማዊ አደረጃጀት ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያን የሳይበር ደህንነት ስጋት ለመከላከልና አደጋ ሲደርስ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት 24 ሰዓት ሙሉ የሚሰራ "Cyber Emergency and Response Team" ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቴክኖሎጂ፣ በአሰራር ስርዓት፣ በህግ እና መመሪያ የተደገፈ ትልቅ የሳይበር ደህንነት ቁመና ላይ እንገኛለንም ብለዋል፡፡ የሳይበር ጥቃት ዓለም አቀፍ ስጋት መሆኑን በመረዳት ከዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የሳይበር ተቋማት ጋር በትብብር መሥራት የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለአጀንዳ 2063 መሳካት ኃላፊነት እንዳለባት ሀገር ግቦችን እውን ለማድረግ ቀጣናዊ ትስስር እንዲፈጠር አበክራ ትሰራለች ብለዋል፡፡ ከለውጡ በፊት በቀጣና ደረጃ ስለ ሳይበር ደህንነት ተወያይተን አናውቅም ነበር ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፤ አሁን ላይ ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ በሚሰጠው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ከቀጣናው ሀገራት ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የኢትዮጵያን የዲጂታል ድንበር የሚጠብቅ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ ዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ህብረት ባወጣው የሳይበር ደህንነት ቁመና ከነበርንበት 26 ነጥብ ወደ 76 ከፍ ብለናል ብለዋል፡፡   ዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ህብረት አማካሪ ዲጂት ኦክታቭራንቶ በበኩላቸው፤ የሳይበር ደህንነት ሥጋትን ለመከላከል የዲጂታል መሠረተ ልማት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የዓለምን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና የሳይበር ደህንነት ቁመና መቀየሩን ገልጸው፤ ዘመኑን የዋጀ የሳይበር ደህንነት መሠረተ ልማት መገንባት ይገባል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ብሎም በኢጋድ ቀጣና የሳይበር ደህንነት ሥጋትን በመከላከልና ለአደጋዎች ምላሽ በመስጠት የባህል፣ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ልዩነት እንዳለ መታዘባቸውንም ገልጸዋል፡፡ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ሥጋትን ለመከላከል ሰፊ መሠረተ ልማት በመገንባት ወሳኝ ሂደት ላይ መሆኗን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሁሉም ነገር ወደ ዲጂታል ስርዓት እየተሸጋገረ መሆኑን ገልጸው፤ ይሄ ደግሞ የሳይበር ደህንነት ስጋትን መከላከል ያስችላል ብለዋል፡፡    
አገልግሎቱ በዲጂታል የታገዘ የትራፊክ አደጋ መረጃ አስተዳደር ሥርዓት ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስረከበ
Jun 26, 2026 228
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት በዲጂታል የታገዘ የትራፊክ አደጋ መረጃ አስተዳደር ሥርዓት ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስረክቧል፡፡ የኢትዮጵያ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት፤ በመንገድ ትራፊክ አደጋ የሚደርሰውን የሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ለመቀነስ በዘርፉ የተቀመጡ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ግቦችን ለማሳካት የሚያስችለውን የግማሽ ዘመን ስትራቴጂ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ያተኮረ አገር አቀፍ ጉባኤ በማካሄድ ላይ ይገኛል።   በዚሁ ጉባኤ ላይ ተቋሙ ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲያለማው የቆየውን በዲጂታል የታገዘ የትራፊክ አደጋ መረጃ አስተዳደር ሥርዓት ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስረክቧል። የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አባሶ እንደገለጹት፤ አዲሱ የቴክኖሎጂ ሥርዓት ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ በዲጂታል የታገዘና ወጥነት ያለው የመረጃ አያያዝ እንዲኖራት ያደርጋል።   ሥርዓቱ በትራፊክ አደጋ መረጃ አያያዝ ላይ ታማኝነትንና ወጥነትን የሚያሰፍን በመሆኑ፣ በሐሰተኛ መረጃዎች ላይ ተመስርተው በአገሪቱ ላይ የሚወጡ ሪፖርቶችን በተጠናከረና ትክክለኛ መረጃ ለመከላከል ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። የመረጃ አያያዝ ሥርዓቱን ዛሬ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ማስረከባቸውን ጠቅሰው በቀጣይ በሂደቱ ላይ ከፌዴራል ፖሊስ ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ጠቅሰዋል፡፡ ሥርዓቱ ከሙከራ እስከ ትግበራ ድረስ ሁለት ዓመታት የፈጀ ሲሆን፣ በተለያዩ ደረጃዎች ላይ የሚገኙ ባለድርሻ አካላትም የሥርዓቱ አጠቃቀም ላይ ስልጠና እንዲወስዱ መደረጉን ጠቁመዋል። ከዚህ ቀደም ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ጥናቶች መደረጋቸውንና በአዲስ አበባ፣ በጅማ፣ በባህር ዳር እንዲሁም በድሬዳዋ ከተሞች ላይ በተደረገው የሙከራ ትግበራ ውጤታማ መሆኑ በመረጋገጡ አሁን ላይ በሁሉም ክልል ከተሞች ተግባራዊ እንዲሆን መዘጋጀቱን ጠቅሰዋል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ርስቱ ይርዳው በበኩላቸው፤ ይህ የመረጃ አያያዝ ሥርዓትን የማዘመን ሂደት አገሪቱ በዲጂታላይዜሽን ዘርፍ የጀመረችው ጉዞ አንዱ አካል መሆኑን ገልጸዋል።   ፖሊስ ወቅታዊ፣ አስተማማኝና ዘመናዊ የመረጃ ሥርዓት ማግኘቱ የትራፊክ አደጋን ከመከላከል አኳያ ሥራውን በእጅጉ የሚያቀልና የመረጃ አያያዙን የሚያዘምን መሆኑን ጠቅሰዋል። አዲሱ ሥርዓት በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ጠቅሰው አገራዊ ፖሊሲዎችንና ውሳኔዎችን በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመስርቶ ለማውጣት ያለው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል። በተጨማሪም አደጋዎችን ከመመዝገብ ባለፈ፣ የአደጋውን መንስኤዎች በትክክል መዝግቦ መፍትሄ ለመፈለግ ዕድል እንደሚሰጥ ጠቁመው በሐሰት የሚወጡ መረጃዎችን በተጨባጭ መረጃ በመከላከል፣ ለቱሪዝም እና ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ጠቁመዋል፡፡ የሰለጠነ የሰው ኃይልና ወደ አንድ የጋራ ቋት የሚገባ የመረጃ ሥርዓት መገንባት እንደሚያስችልም ጠቅሰዋል፡፡ አገሪቱ የራሷ የሆነ ብሔራዊ የመረጃ ቋት እንዲኖራት ያደረገ በመሆኑ፣ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይህንን ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት በፍጥነት ወደ ሥራ የማስገባትና የመተግበር ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በክልሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jun 26, 2026 211
ዱራሜ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የዱራሜ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ቋት የተለያዩ አገልግሎቶችን በመስጠት የማህበረሰቡን ጊዜና ጉልበት ከመቆጠብ በተጨማሪ ብልሹ አሰራርን በመከላከል ረገድ በጎ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።   በክልሉ በሚገኙ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት ተገንብተው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው በዱራሜ ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው 6ኛው መሆኑን ጠቅሰዋል። የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ በበኩላቸው፤ የመንግስት አገልግሎትን በማዘመን ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ስራ በልዩ ትኩረት እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።   አገልግሎቱን በሌሎች መዋቅሮች በማስፋት የማህበረሰቡን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አመላክተዋል። የዱራሜ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ነፃነት አፌቦ፤ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል በመንግስታዊ አገልግሎቶች ላይ ይስተዋል የነበረን የአሰራር ችግር ይቀርፋል የሚል እምነት እንዳላቸው አመላክተዋል።በማእከሉ ስራ መጀመር መደሰታቸውንም ገልጸዋል።   መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ አገልግሎቶችን በአንድ ቋት በመሰብሰብ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑ እንግልትን ያስቀራል ያሉት ደግሞ የከተማው ነዋሪ አቶ በየነ አርፊጮ ናቸው። በስነ ስርአቱ ላይ የክልል ፣ የዞንና የዱራሜ ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ስፖርት
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ወሳኝ ድል ተቀዳጅቷል
Jun 26, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ አርባምንጭ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሰመረ ሀፍታይ በሰባተኛው ደቂቃ ግቧን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከሶሶት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ45 ነጥብ ደረጃውን ከ16ኛ ወደ 14ኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን ያስመዘገበው ወልዋሎ በሊጉ የመቆየት እድሉን ይበልጥ አስፍቷል። በአንጻሩ በሊጉ 16ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርባምንጭ ከተማ በ35 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። አርባምንጫ ከተማ ከሊጉ መውረዱ ይታወቃል። ዛሬ ቀን ላይ በተደረጉ የ37ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና መቀሌ 70 እንደርታን 3 ለ 0 አሸንፏል። ይህን ተከትሎም መቀሌ 70 እንደርታ ከአርባምንጭ ከተማ በመቀጠል ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረደ ሁለተኛ ቡድን ሆኗል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0፣ ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፈዋል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ የአፍሪካ የተስፋና የብልፅግና ተምሳሌት እየሆነች ነው
Jun 26, 2026 41
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በስንዴ ልማት፣ በከተማ ልማት እና ሌሎችም መስኮች የአፍሪካ የተስፋና የብልፅግና ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል።   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላትም ዛሬ ከአራዳ ክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን በአራት ኪሎ አካባቢ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ የማኖር ሥራ በኢትዮጵያ በተጨባጭ ትላልቅ ውጤቶችን እያስመዘገበ የሚገኝ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ባለፉት አምስት ዓመታት የምክር ቤቱ አባላት ከአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ችግኝ የተከሉበት ቦታ በአሁኑ ወቅት ለምልሞ «ጫካ» መሆን መቻሉን ጠቅሰው፥ ይህም መርሃ ግብሩ በተግባር ውጤት እያሳየ ለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል። ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ በዓለም ላይ የሰውን ልጅ እየፈተኑ ካሉ ጉዳዮች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ ዋነኛው መሆኑን የጠቀሱት ተጠሪ ሚኒስትሩ፥ ይህ የዓለም አየር ንብረት ለውጥ የመጣው በሰው ልጅ አላስፈላጊ የተፈጥሮ ጣልቃ ገብነት ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል።   ይህንን ችግር ለመቅረፍና ለመቀነስ በዓለም መድረኮች ላይ የተለያዩ ስምምነቶች፣ ውይይቶችና ኮንፈረንሶች እየተካሄዱ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ግን በተግባር የተለየ ታሪክ ለዓለም እየጻፈች ትገኛለች ብለዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት በተደረገው ከፍተኛ ሕዝባዊ ንቅናቄ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከልና ተንከባክቦ በማጽደቅ ለተለያዩ ዓላማዎች ማዋል መቻሉን ገልጸዋል። ዘንድሮ ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍልና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተደራጀ መልኩ የራሳቸውን ታሪካዊ ድርሻ ለማበርከት በንቅናቄው እየተሳተፉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ ሀገሪቱ በምግብ ራስን የመቻል ግብንና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የጀመረችውን ሥራ በከፍተኛ ሁኔታ እየደገፈ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም ከሰባት ዓመታት በፊት የተተከሉ ዘርፈ ብዙ ተክሎች ዛሬ ላይ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ከዚህም የተነሳ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕልና ሎሚ ያሉ የተለያዩ ምርቶች እንደየአካባቢው የግብርና ሥርዓተ ምህዳር ከፍተኛ ምርት እያስገኙ ነው ያሉት ተጠሪ ሚኒስትሩ አቮካዶ ከሀገር ፍጆታም ባለፈ ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑን አብራርተዋል። በሌላ በኩል አረንጓዴ ዐሻራ ባስገኘው ለውጥ የአበባ እፅዋቶች በመብዛታቸው በሀገሪቱ ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና የማር ምርት ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን አንስተዋል። በመርሃ ግብሩ ከተፈጥሮ መጎዳት ጋር ተያይዞ የመጣውን በረሃማነትና ድርቅን የመግታትና የመቆጣጠር ሥራ መሠራቱን ጠቁመዋል። የአፈር መሸርሸርን ማስቆም የተቻለ ሲሆን፣ የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር የውሃ ሀብት በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ የጠፉ ምንጮችና ሐይቆችም መልሰው እያገገሙ ይገኛሉ ብለዋል። ይህ የውሃ ሀብት ማደግ ደግሞ በሀገሪቱ የመስኖ ልማት ሥራ እንዲጨምር በማድረጉ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው ሥራ እጅግ ውጤታማ እንዲሆን አስችሏል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ፣ በከተማ ልማት እንዲሁም በስንዴ ልማትና በሌሎችም መስኮች ለአፍሪካውያን ጭምር አዲስ የተስፋና የብልጽግና ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን ገልጸዋል።   “ተስፋን እንትከል” የሚለው የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መሪ መልክትም የተቀረጸው ከዚህ በመነሳት መሆኑን ጠቅሰው፥ ተስፋ ያላት ሀገር፣ ተስፋ ያለው ሕዝብና ተስፋ ያለው ትውልድ እየተገነባ ነው ብለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለነገ የሚደረግ ትልቅ ኢንቨስትመንትና የነገ ተስፋ መሆኑን በመግለፅ፥ በአሁኑ ወቅት የችግኝ ተከላ ሥራ የሕዝብ የሥራ ባህልና ተቋማዊ አሠራር እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች በየቤታቸው፣ በየአካባቢያቸውና በየማሳቸው ጭምር ችግኝ ማፍላትና መትከል መደበኛ ሥራቸው መሆኑን በማንሳት። የምክር ቤት አባላት የጀመሩትን የችግኝ ተከላ ሥራ ክረምቱን ወደ መረጣቸው ማኅበረሰብ ሲመለሱ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ መሪ ያሰኘው አረንጓዴ አሻራ፡ሌላው የኢትዮጵያ የማከናወን አቅም ማሳያ
Jun 26, 2026 129
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ያከናወነችው የ"አረንጓዴ ዐሻራ" ንቅናቄ የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አገራዊ ግብን ከማሳካት ባለፈ፣ሀገሪቱን በአፍሪካና በዓለም አቀፍ መድረክ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ግንባር ቀደም መሪ እንድትሆን አስችሏታል። ይህ ታላቅ የተፈጥሮ ጥበቃ ዘመቻ የሀገር ውስጥ የአካባቢ ሚዛንን ከመጠበቅ አልፎ፣ድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲያዊ ትስስርን ማጠናከሪያ ስትራቴጂካዊ መሣሪያ እስከመሆን ደርሷል። ይህ ተሞክሮ የሚያሳየው የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ ተራ የደን ልማት መርሃ ግብር ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካና ከዚያም ባሻገር ለሚታየው የአየር ንብረት መዛባትና የምድረ በዳነት መስፋፋት ተጨባጭ መፍትሔ ይዛ የቀረበችበት መሆኑን ነው። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ሀገራት ችግኞችን በሕዝብ ንቅናቄ የመትከልና የማጽደቅን ስኬታማ የፖሊሲ አፈጻጸም እንደ ትልቅ ልምድ የቀሰሙበት ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከሀገር ውስጥ ባለፈ ለጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ናይጄሪያ እና ሩዋንዳን ጨምሮ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ችግኝ ልካለች። ይህ አረንጓዴ አሻራ የፓን አፍሪካን የአጋርነት መንፈስ አዲስ መገለጫ እና ጉዳዩ የአፍሪካ አጀንዳ እየሆነ መምጣቱን አመላካች ሲሆን አፍሪካውያን በአካባቢ ጥበቃ ዘላቂ ትብብር መፍጠር እንዳለባቸውም የሚያስገነዝብ ነው። በዚህም ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዙሪያ ያሳየችው ጥረት የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የምታደርገውን ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የአካባቢ ጥበቃን ለቀጣናዊ ሰላምና ትብብር መሠረት ማድረግ እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ታላቅ ስኬት ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም በተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ አሻራ በአፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ሀገር በቀል ምላሾች መካከል በዋናነት የሚጠቀስ ነው። ዘንድሮም የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ስራ ላይ በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባሻገር ለምግብ ዋስትና ትልቅ አቅም እየሆነ ነው
Jun 26, 2026 123
ሠመራ፤ ሰኔ 19/2018(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባሻገር ለምግብ ዋስትና ትልቅ አቅም መሆኑን የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በገቢ ራሱ ዞን አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ሳቡሬ ቀበሌ አስጀምረዋል።   በዚሁ ሁነት ላይ እንደተናገሩት እንደ ሀገር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው። በአፋር ክልልም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባሻገር ለምግብ ዋስትና መሰረት ሆኖ እያገለገለ መሆኑን አንስተው ዘንድሮም ልማቱ በተጠናከረ መልኩ ይከናወናል ብለዋል። በዚህም ከ12 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አንስተው፤ 60 ከመቶ የሚሆኑት የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። ለእቅዱ መሳካት የክልሉ ህዝብ አሻራውን በማኖር በልማቱ ጠንካራ ተሳትፎ እንዲያደርግም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።   የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ያሲን ዓሊ በክልሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 41 ሚሊየን ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰዋል። በዘንድሮ ዓመትም በ6 ሺህ 600 ሄክታር መሬት ላይ ከ12 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር  የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና እያበረከተ ነው  
Jun 26, 2026 317
ድሬደዋ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና እያበረከተ መሆኑን የድሬዳዋ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በድሬደዋ አስተዳደር ቢሻን በሔ ገጠር ቀበሌ የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄዷል።   የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከንቲባ ከድር ጁሃር እና የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በቢሻን በሔ ቀበሌ ችግኞችን በመትከል አስጀምረዋል። ከንቲባ ከድር በወቅቱ፤ በአስተዳደሩ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በተከናወኑት ተግባራት የጎርፍ ስጋትን ማስቀረትና የግብርና ምርታማነት ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በዚህም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ ህብረተሰቡ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እንዲሸጋገርና የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።   ውጤቶቹን ለማዝለቅም በዘንድሮው ክረምት ችግኞች የመትከልና የመንከባከብ ስራ በንቅናቄ እንደሚከናወን ተናግረዋል። ተግባሩም ለድሬደዋ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ህብረተሰቡ ባህሉ አድርጎ መስራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የአስተዳደሩ ግብርና፣ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ስኬታማ እያደረገው መሆኑን ተናግረዋል።   በተለይም ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉት 13 ነጥብ 6 ሚሊዮን ችግኞች የአስተዳደሩን የደን ሽፋን ከ18 በመቶ ወደ 36 በመቶ ከፍ ማድረጉን አንስተዋል። እነዚህ ለደንና ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች የአካባቢውን ስነምህዳር በመቀየርና ምርታማነትን በማሳደግ የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ አስችለዋል ብለዋል።   ዘንድሮ ከሚተከሉት 5 ሚሊዮን ችግኞች ውስጥ 60 በመቶ የሚሆኑት ለምግብነት የሚውሉ መሆናቸውን ገልጸው፤ ከነዚህም ውስጥ 1ሺህ 200 ሄክታር መሬት በብርትኳንና ፓፓያ በክላስተር የሚለማ መሆኑን ገልጸዋል። በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት አፈጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የቀበሌው ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 12499
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 8911
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 7729
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 7629
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
ከተጽዕኖ ፈጣሪነትና ተደማጭነት መጎልበት እስከ የአኅጉር ድምጽ መሆን - የኢትዮጵያን ታላቅነት የገለጠው የዲፕሎማሲው ዘርፍ ስኬት  
Jun 25, 2026 1175
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቷ የፓን አፍካኒዝም ንቅናቄን በማንሳት አኅጉራዊ ተቋማት እንዲመሠረቱ ፊታውራሪ ከመሆን ጀምሮ ለጎረቤቶቿ ሰላም ጉልኅ ሚና ተጫውታለች፤ አሁንም ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔን እያሰረጸች በርካቶች እንዲጋሯት አድርጋለች። እንደ ሀገር ከለውጡ መንግሥት ወዲህ ከተገኙ በርካታ ትላልቅ ስኬቶች መካከል በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው አንዱ ነው። ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የለውጡ መንግሥት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ዋነኛ መለኪያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ነው። የኢትዮጵያ ሁኔታዎችን የማሰብ፣ የመፈለግና የመከወን ሂደት ንጥል (ለራስ ብቻ የሚል) ሳይሆን፤ በወንድማማችነት/እህትማማችነት ዕሳቤ በጋራ ማደግን ያነገበ ነው። ይህ ሂደቷም በበርካታ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ እንዲሁም አኅጉር አቀፍ ተቋማት ተወድሷል። በዚህም ሐሳቦቿ ቅቡል ሲሆኑ ተመልክተናል። ኢትዮጵያ የ#BRICS አባል መሆን መቻሏ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ይህም ተሰሚነቷን ያረጋገጠ ማስረጃ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ተያያዥ ጉዳዮች ዘርፈ-ብዙ ጥቅም በማስገኘት የበለጸገች ኢትየጵያን ዕውን የማድረግ ጉዞው ያፋጥናል። ወዲህ ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልና አፍሪካን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና መመረጧም የአኅጉሪቱ ድምጽ መሆኗን ይነግረናል። ዓለም አቀፍ ብሎም አኅጉር አቀፍ የሆኑ በርካታ ኮንፈረንሶችም በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እንዲካሄዱ መደረጉ አንድምታው ብዙ ነው። በብቃት ማስተናገዷ ደግሞ ሌላኛው ጥንካሬዋ። ሌላው የሀገራችንን የተጨበጠ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት የሚገልጽልን፤ የዓለም የዓየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን (COP32) እንድታዘጋጅ መመረጧ ነው። ይህን ትልቅ ዕድል በርካቶች ስለተመኙት አላገኙትም፤ ኢትዮጵያ ግን ዜጎቿን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባከናወነችው ያላሰለሰ ትጋት አግኝታዋለች። ግጭት ባለባቸው የቀጣናው ሀገራትም በመንግሥታቱ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት ሥር ከምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባለፈ፤ በግሏ የሰራችው ብዙ ነው። ከራሷ አልፋ ለጎረቤቶቿ ዘብ መሆኗ፤ በአብሮነት መኖርን እና በጋራ ማደግን በተግባር የገለጠች ሀገርም ያደርጋታል። ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ በሚለው ቅድሚያ ለሀገር በቀል ዕውቀቶች በሩን ክፍት ባደረገው ትጋቷም፤ በበርካታ የአኅጉሪቱ ሀገራት ዘንድ ምሥጋና አስችሯታል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲዋም በተለያዩ ሀገራት በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎቿን ከሀገራቱ እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመነጋገር በተሳካ ሁኔታ ልጆቿን ወደ ዕቅፏ መልሳለች፤ በቅርቡ በሳዑዲ ዓረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምኅረት ዐዋጅ እንዲሰጣቸው መደረጉ አንድ ማሳያ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን ጨምሮ በተለያዩ አኅጉራት በሚገኙ ሀገራት መሪዎችና ተወካዮች ዘንድ በስፋት የተመረጠችና የተጎበኘች ሀገር መሆኗን ማስታወስ ተገቢ ነው። ከጉብኝት ባለፈ ትላልቅ ስምምነቶችም የተፈራረመች መሆኗን ልብ ማለት ይገባል፤ ይህም የምታነሳውን ሐሳብ ገዥነትና የአፍሪካ መግቢያ በር መሆኗን ያሳያል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ መሆኑን መረዳት ይገባል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድርድር ሂደት የተጎናጸፈችው የዲፕሎማሲ ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መነቃቃት መፍጠሩንም ማጤን ያስፈልጋል። ይህ የተሳካው ሀገሪቱ ኢትዮጵያ መንገዷም የጋራ ልማትን የሰነቀ ዕውነት በመሆኑ ነው። በቀጣይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለአንዲት ሀገራቸው አምባሳደር በመሆን፤ የዲፕሎማሲውን ሥራ በይበልጥ ማገዝ ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ካልሠሩ ማን ለሀገራቸው ሊሠራ ይችላል?
እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል?
Jun 25, 2026 827
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በዝምታ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት፤ የጨጓራ፣ አንጀትና ጉበት ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሚፍታህ ደሊል ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የጉበት ጤናን እንዴት መጠበቅ እንደሚቻል፣ ለጉበት ጤና መታወክ ስለሚያጋልጡ ጉዳዮች፣ ስለጉበት ስብ (ቅባት) እንዲሁም ሕክምናው ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል። · በሰው ልጅ ሕይዎት (ሠርካዊ እንቅስቃሴ) ውስጥ የጉበት ሚና ምንድን ነው? ዶክተር ሚፍታህ እንደገለጹት፤ ጉበት በሰውነታችን ውስጥ ኪሚገኙ ትላልቅ የውስጥ አካል ክፍሎች (ኦርጋኖች) አንዱ ነው። ከ1 ሺህ በላይ ተግባራትን የሚያከናውን ትልቁ እና ባተሌ የሆነ የአካል ክፍል መሆኑንም አስረድተዋል። የኪንታሮት በሽታ መንስዔ ይታወቃል? ካንሰር እንዴት ይከሰታል? · ለጉበት ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ይታወቃሉ? ለጉበት ህመም አጋላጭ ከሆኑ መንስዔዎች መካከል፤ ቫይረሶች (ሄፓታይትስ ቢ፣ ሄፓታይትስ ሲ) እንዲሁም አልኮል (ከፍተኛ መጠን ያለው አልኮል መጠጣት) መሆናቸውን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅት ደግሞ በስፋት የሚስተዋለው አጋላጭ መንስዔ የጉበት ስብ መጨመር መሆኑንም በአጽንዖት ገልጸዋል። በእኛ ሀገር ደረጃ ከሚከሰቱ የጉበት ህመሞች 50 በመቶው በሄፓታይትስ ቢ ምክንያት የሚከሰት ነው ይላሉ ዶክተር ሚፍታህ። ከ15 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የጉበት ህመም የሚከሰተው ደግሞ በአልኮል ምክንያት መሆኑን ነው ያስረዱት። እንዲሁም በሄፓታይትስ ሲ ምክንያት የሚከሰተው የጉበት ህመም ከላይ ከተገለጹት ቀጥሎ በሦስተኛነት እንደሚቀመጥም አመላክተዋል። አሁን አሁን ደግሞ ይላሉ ዶክተር ሚፍታህ፤ በሥራም ሆነ ለመዝናናት ለረጂም ሠዓታት መቀመጥን ተከትሎ የጉበት ስብ (ቅባት) በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋና ለጉበት ህመም እያጋለጠ መሆኑን አስገንዝበዋል። · የጉበት ፋት (ስብ፣ ቅባት) ለጉበት ህመም የሚያጋልጥበት ምክንያት ምንድን ነው? የጉበት ስብ በተለያዩ ሀገራት (በእኛም ሀገር በትላልቅ ከተሞች) በስፋት የሚከሰት ነው ያሉት ዶክተር ሚፍታህ፤ የጥናት ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከዓለም ሕዝብ 30 በመቶው (1/3ኛው ወይም ከ2 ቢሊየን በላይ ያህሉ) የጉበት ስብ ሊኖርበት ይችላል ይላሉ። በእርግጥ ሁሉም የጉበት ስብ ወደ ከፍተኛ የጉበት ቁስለት ይሸጋገራል ማለት እንዳልሆነ ገልጸው፤ የጉበት ስብ ካለባቸው መካከል ከ10 እስከ 15 በመቶ ያህሉ ብቻ ስቡ ከመብዛቱ የተነሳ ጉበቱን ማቁሰል እንደሚጀምር አስገንዝበዋል። ይህ ቁስለት ደግሞ እየዳነ እንደገና እያገረሸ ጠባሳ እየፈጠረ ይሄድና ጉበት ሥራውን ማከናወን የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ የጉበት መድከም ይከሰታል፤ ሰዎችም ጉዳት ይደርስባቸዋል ይላሉ። የጉበት ስብ መንስዔም፤ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ አለማድረግ (መቀመጥን ማዘውተር)፣ ፋስት ፉድ ማዘውተር (የተጠበሱ ምግቦች፣ በርገር፣ ችብስ፣ ዘይት የበዛባቸው ምግቦች) እንዲሁም ከፍተኛ ስኳር ያላቸው ለስላሳ መጠጦች፣ አልኮል መሆናቸውን አብራርተዋል። · የጉበት ስብን እንዴት መከላከል ይቻላል? የጉበት ስብ ከፍ እያለ ሲሄድ በአልትራሳውንድ እንደሚታይ (ትንሽ ከሆነ አይታም) የገለጹት ዶክተር ሚፍታህ፤ እስካሁን ክትባት እንደሌለው አረጋግጠዋል። ይህ ኬዝ እንቅስቃሴ ባለማድረግ፣ ኮምፒውተርም ሆነ ቴሌቪዥን ለማየት ረጂም ሠዓት በመቀመጥና በውፍረት መጨመር የሚከሰት መሆኑን ጠቁመው፤ መከላከያ መንገዱም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ (ቢያንስ በሳምንት እስከ 150 ደቂቃ በእግር መሄድ (ዎክ ማድረግ) ወይም በቀን ለ30 ደቂቃ ዎክ ማድረግ) መሆናቸውን ዘርዝረዋል። በተጨማሪም በፋብሪካ ፕሮሰስ የተደረጉ የታሸጉ ምግቦችን አለማዘውተር፣ ከስኳር ነጻ የሚሉ የሚበሉም ሆነ የሚጠጡ ነገሮችም ቢሆኑ በቀጥታም ባይሆን በሌላ መንገድ ጣፋጭ ስለሚኖራቸው አለማዘውተር፣ የተጠበሱ እንደ ችብስ እና መሰል ያሉ ምግቦችንም አለማዘውተር እንደሚገባ መክረዋል። ከልክ ያለፈ ውፍረት እንዳይኖር ማድረግም ለጉበት ስብ ተጋላጭነትን እንደሚቀንስ አስረድተዋል። · የጉበት በሽታ ምልክቶች እንደ ኬዙ ቢለያይም ጉበት 80 በመቶ ያህል ክፍሉ እስከሚጎዳ ምልክት ላያሳይ እንደሚችል ዶክተር ሚፍታህ ይገልጻሉ። 15 ወይም 10 በመቶ ጤናማ ክፍሉ ሲቀር (ከ85 በመቶ በላይ ክፍሉ በጣም ሲጎዳ) አንዳንድ ምልክቶች ሊያሳይ እንደሚችል ገልጸዋል። እነዚህ ምልክቶችም፤ ሆድ ላይ ውኃ መፍጠር (አሳይተስ)፣ ደም ማስመለስ መሆናቸውን እና በዚህ ወቅት የጉበት ንቅለ ተከላ ካልሆነ መፍትሔ እንደሌለው አንስተዋል። በአንጻሩ ግን፤ ‘አኪዩት ሄፓታይትስ’ የሚባለው ወይም አንድ ቫይረስ ጉበትን ሲያጠቃ ወዲያውኑ ሕክምና ይደረግለታል ሙሉ በሙሉም ይድናል ብለዋል።በዚህ ወቅት የሚየሳየው ምልክትም የዐይን ቢጫ መሆን፣ በቀኝ ደረት ሥር የውጋት ስሜት መኖር፣ ከፍተኛ ድካም መኖር፣ የምግብ ፍላጎት አለመኖር (ምግብ አስጠላኝ ማለት)፣ ማቅለሽለሽ እንዲሁም ማስመለስ መሆናቸውን አብራርተዋል። · የጉበት በሽታ አሳሳቢ ነው? የጉበት በሽታ በዓለም አቀፍ ደረጃም በተለያዩ ሀገራት ከ1 እስከ 10 ገዳይ (አሳሳቢ) ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል መሆኑን ዶክተር ሚፍታህ አስረድተዋል። በእኛ ሀገር ደረጃም የጉበት ካንሰር ከ3 እስከ 4 ገዳይ ተብለው ከሚጠቀሱ በሽታዎች መካከል መሆኑን ነው የጠቆሙት። በዓለም በየዓመቱ እስከ 3 ሚሊየን ሰዎች በጉበት በሽታ እንደሚሞቱ ገልጸው፤ ይህ አኃዝ አሳሳቢነቱን ያስረዳል ብለዋል። ምንም እንኳን ቀድሞ በሚወሰድ ክትባት (ለሄፓታይትስ ቢ) ከተከሰተ በኋላም በሚወሰድ መድኃኒት (ለሄፓታይትስ ሲ) አበረታች ውጤቶች ቢኖሩም፤ የጉበት ስብ (ቅባት) ግን በሀገራችንም ሆነ በዓለም ላይ በተለይም በከተማ ነዋሪዎች ዘንድ በስፋት እየተስተዋለ ያለ በመሆኑ አሳሳቢ ነው ብለዋል። · የጉበት በሽታ በተለይም በየትኞቹ የዕድሜ ክልሎች ላይ በስፋት ይከሰታል? የጉበት በሽታው ዓይነት በስፋት የሚከሰትበትን ዕድሜ እንደሚወስን ጠቁመው፤ በዚህም መሠረት ለምሳሌ፡- ሄፓታይትስ ቢ ከ30 ዓመት በታች ባሉ ሰዎች ላይ፣ ሄፓታይትስ ሲ ከ20 እስከ 40 ዓመት (አንዳንድ ጊዜ ከ40 ዓመት በላይ ባሉ ሰዎች ላይም ሊከሰት ይችላል)፣ የጉበት ስብ (ቅባት) ደግሞ ከ40 ዓመት በላይ ባሉ ሰዎች ላይ በስፋት እንደሚስተዋል ያስረዳሉ። · የጉበት በሽታን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? ዶክተር ሚፍታህ እንዳሉት የጉበት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የቻልባቸው የተለያዩ አማራጮች አሉ። ለምሳሌ፡- የሰውነት ክብደት (ውፍረት) ከልኩ እንዳያልፍ መቆጣጠር፣ ረጂም ሠዓት አለመቀመጥ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር፣ አልኮል አለመጠጣት (በቀን ከአንድ ቢራ በላይ መጠጣት ለጉበት ስብ ያጋልጣል)፣ ጣፋጭ ምግብና መጠጦችን መቀነስ (ጭራሽ አለመጠቀም ቢቻል)፣ ዘይት የበዛባቸውና የተጠባበሱ ምግቦችንም አለማዘውተር የሚሉትን አንስተዋል። በተጨማሪም በእኛ ሀገር ቀዳሚው የጉበት በሽታ ሄፓታይትስ ቢ መሆኑን በመግለጽ፤ ለዚህም ከ95 በመቶ በላይ የመከላከል ዐቅም ያለው ክትባት ስላለው ሦስት ጊዜ በመከተብ አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠዋል። · የሕክምና አማራጮች አሉት? ሄፓታይትስ ቢ ተከስቶ ጉበቱን ማቁሰል ከጀመረም የሚሰጥ ውጤታማ መድኃኒት መኖሩን አስታውቀዋል። ይህ መድኃኒት ምናልባት ዕድሜ ልክ ሊወሰድ ይችላል ነገር ግን ቁስለቱንም ሆነ ቫይረሱን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ነው ያሉት። ሄፓተይትስ ሲ ከሆነ ደግሞ በጣም ውጤታማ የሆነ ለሦስት ወር የሚሰጥ መድኃኒት አለ ብለዋል። ጠባሳ ከሆነ እና ከ85 በመቶ በላይ የሚሆነው የጉበት ክፍል ከተጎዳ (ከተበላሸ) ግን በውጭ ሀገር የጉበት ንቅለ ተከላ ማድረግ አስገዳጅ ይሆናል ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ ተላላፊ ካልሆኑ የጉበት በሽታዎች አንዱ እና አሁን በስፋት እየተስተዋለ ያለውን የጉበት ስብ (ቅባት) ጨምሮ የጉበት ጤናን ለመጠበቅ፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በየቀኑ ማድረግን መክረዋል። በዓመት አንድ ጊዜ የጤና ምርመራ በማድረግ ያሉበትን ሁኔታ ማወቅም ቢለመድ ሲሉ ይመክራሉ። በወቅቱ ከተደረሰብት የጉበት በሽታ መዳን እንደሚችል ገልጸው፤ በቸልተኝነት ወደ ተወሳሰበ ደረጃ ከፍ ካለ ግን እስከ ጉበት ካንሰር ሊደርስ እንደሚችልም አመላክተዋል።  
የጤና ነገር
Jun 24, 2026 1536
በዮሐንስ ደርበው የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ከተከሰተ በኋላስ የሚድንበት ዕድል ይኖራል? · ኪንታሮት እንዴት ይከሰታል? አጠቃላይ የቀዶ ጥገና ሐኪም የሆኑት ዶክተር ቤተልሔም አበራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በፊንጢጣ ውስጥ የሚገኙ በጤናማ መንገድ ፊንጢጣ እንዲዘጋ (‘ኩሽን’ እንዲሆን) የሚያደርጉ ደም ሥሮች በተለያየ ምክንያት ሲያብጡ ኪንታሮት (ሄሞሮይድ) ተከሰተ እንደሚባል አስረድተዋል። · የኪንታሮት በሽታ መንስዔ ይታወቃል? እንደ ሕክምና ባለሙያዋ ገለጻ ለኪንታሮት በሽታ መንስዔ ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል፤ የሰገራ ድርቀት በዋናነት ይነሳል። በተጨማሪም ይላሉ፤ በተለይም ሴቶች ላይ በእርግዝና ወቅት የጽንሱ መጠን (ክብደት) እየጨመረ በሚሄድበት ጊዜ ወደ መቀመጫ በሚያደርገው ጫና ምክንያት በፊንጢጣ ውስጥ የሚገኙ የደም ሥሮች እንዲያብጡ በማድረግ ለኪንታሮት መከሰት መንስዔ ይሆናል። በአሁኑ ጊዜ በስፋት ለሚከሰት የኪንታሮት በሽታ በመንስዔነት የሚነሳው ከመጠን ያለፈ ውፍረት መጨመር መሆኑንም ጠቁመዋል። ይህም ውፍረት ወደ መቀመጫ ጫና በማሳደር በፊንጢጣ ውስጥ ያሉ የደም ሥሮች እንዲያብጡ በማድረግ ኪንታሮት እንዲከሰት ያደርጋል ነው ያሉት። በሌላ በኩል እንደ ሥራ ባሕርያቸው ለረጂም ሠዓታት የሚቀመጡ ሰዎች ስለማይንቀሳቀሱና ይህን ተከትሎም ለድርቀት ስለሚጋለጡ ለኪንታሮት በሽታ ይዳረጋሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። ከአመጋገብ ዘይቤ ጋር በተያያዘም፤ በቂ ውኃ አለመጠጣት እና በፋይበር የበለጸጉ ምግቦችን አለማዘውተር ለድርቀት ስለሚዳርግ የኪንታሮት በሽታ እንዲከሰት ያደርጋል ብለዋል። ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) የጡት ካንሰርን መከላከል ይቻላል? · የኪንታሮት በሽታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ ያለው ለምንድን ነው? ኪንታሮት የተለመዱ (‘ኮመን’) ከሚባሉ የቀዶ ሕክምና በሽታዎች መካከል አንዱ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ቤተልሔም፤ በትክክል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን መረጃ ለጊዜው መግለጽ ባይቻልም በዓለም አቀፍ ደረጃ እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ የኪንታሮት ተጠቂ እንደሆነ ጠቁመዋል። እዚህ ላይ ልብ መባል ያለበት ጉዳይ የኪንታሮት በሽታ ከቦታ ቦታ ከሀገር ሀገር እንደሚለያይ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለዚህም ምክንያቱ ከውፍረት እና ለድርቀት ከሚያጋልጡ አመጋገቦች መዘውተር ጋር የተያያዘ በመሆኑ ነው ይላሉ። ለምሳሌ፡- በጣም ወፍራም ሰዎች በሚበዙባቸው እና ለድርቀት አጋላጭ ምግቦች በሚዘወተሩባቸው አካባቢዎች የኪንታሮት ተጋላጭነት ከፍተኛ ነው ይላሉ። የኪንታሮት በሽታ እየጨመረ (እየተስፋፋ) የሚሄድበት ምክንያትም ከአኗኗር ዘይቤ ጋር እንደሚያያዝ ገልጸው፤ ለምሳሌ አብዛኛውን ጊዜ ቁጭ ብሎ (ተቀምጦ) ማሳለፍ ለኪንታሮት አጋላጭ መንስዔ ነው ብለዋል። በተለይም ቢሮ አካባቢ የሚሠሩ ሰዎች ለበርካታ ሠዓታት ስለሚቀመጡ፣ ሥራ ሲበዛባቸውም ወደ መጸዳጃ ቤት መሄድ ባለባቸው ሠዓት ባለመሄድ (የሚሄዱበትን ጊዜ ስለሚያራዝሙ፣ ቆይ ይችን ልጨርስ…ትንሽ…የተወሰነ ደቂቃ እያሉ ማራዘም) ሰገራን ለድርቀት ያጋልጣል፤ ይህም የደም ሥሮች እንዲያብጡና ከፊንጢጣ ውጭ እንዲወጡ በማድረግ ለኪንታሮት መከሰት ያጋልጣል ብለዋል። · የኪንታሮት በሽታ ምልክቶች በፊንጢጣ ላይ ዕብጠት መኖር፣ መድማት፣ ማሳከክ እና የህመም ስሜት መኖር ከምልክቶቹ መካከል መሆናቸውን ዶክተር ቤተልሔም ያብራራሉ። የኪንታሮት በሽታ የውስጠኛው እና የውጨኛው ተብሎ እንደሚከፈል በመግለጽ፤ የበሽታው ደረጃም ከአንድ እስከ አራተኛ እንደሚመደብ ያስረዳሉ። ይህን ሲያብራሩም፤ በውስጠኛው የኪንታሮት በሽታ ባብዛኛው ህመም አይኖርም፣ የፊንጢጣ ደም ሥሮች ዕብጠትና መድማት ይኖራል፤ በውጨኛው የኪንታሮት በሽታ ግን የህመም ስሜት ይኖራል ይላሉ። · የኪንታሮት በሽታ ደረጃዎች ደረጃዎቹን በተመለከተ ሲያስረዱ፤ ምልክቶቹን እንዳስተዋሉ ቶሎ ወደ ሕክምና ባለመሄድ ከአንደኛ ወደ ሁለተኛ ከዚያም ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ እየተባባሰ እንደሚሸጋገር ገልጸዋል። ስለዚህ ሰዎች ምልክቶቹን እንዳዩ ቢታከሙ ደረጃው ከፍ ሳይል በሽታውን የመግታት ዕድል ይኖራቸዋል ነው የሚሉት። የመጀመሪያ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በዚህ ወቅት የኪንታሮት ህሙማን እንኳን የዕብጠቱን መኖር ባብዛኛው በእጃቸውም ነክተው እንደማያውቁት እና የመድማት ምልክት ሊኖር እንደሚችል ተናግረዋል። ሁለተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በዚህኛው ደረጃ ደግሞ ህሙማኑ በሚጸዳዱበት ወቅት ዕባጩ ወደ ውጭ እንደሚወጣ እና ሲጨርሱ በራሱ ጊዜ ዕባጩ ወደ ቦታው እንደሚመለስ አስገንዝበዋል። ሦስተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በሽታው ያለባቸው ሰዎች በሚጸዳዱበት ወቅት ወደ ውጭ የሚወጣውን ዕባጭ በእጃቸው ወደ ውስጥ ካላስገቡት በራሱ ጊዜ የማይመለስበት ደረጃ መሆኑን ይገልጻሉ። አራተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ ይህ ደረጃ ዕባጩ ከፊንጢጣ ውጭ ይወጣና ተገፍቶም ወደ ውስጥ መግባት የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታ፤ ያለ ቀዶ ሕክምና ሰዎች እቤታቸው እንዲያደርጉ የሚመከሩትን ሁኔታዎች በአግባቡ ካደረጉ ወደ ቀጣዩ ደረጃ እንዳይሸጋገር ማድረግ ይቻላል ይላሉ። · በወቅቱ ካልታከመ በአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ኪንታሮትን ከላይ በተገለጹ የኑሮ እና አመጋገብ ዘይቤዎች ማስተካከል እንደሚቻል (ወደ ቀጣዮቹ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ሳይሸጋገር ባለበት እንዲቆይ) ማድረግ እንደሚቻል ያስረዳሉ። ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ከደረሰ ግን የቀዶ ሕክምና እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ ይህ ደግሞ ጥቅምም የጎንዮሽ ጉዳትም እንዳለው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም በመጀመሪያዎቹ ደረጃዎች ካልታከመ እና ወደ መጨረሻዎቹ ደረጃዎች ከደረሰ ከፍተኛ የደም መፍሰስ እንደሚኖረውና ይህም ከሰው ደም እስከመለገስ ሊያደርስ እንደሚችል ይገልጻሉ። ወደ ውጭ ወጥተው በሚቀሩ የፊንጢጣ ደም ሥሮች ውስጥ የደም መርጋት ሊያጋጥም እንደሚችልና ይህም ከፍተኛ ህመም እንደሚያመጣ ተናግረዋል። በዚህም ድንገተኛ ሕክምና የመፈለግ ደረጃ ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ነው ያመላከቱት። · የኪንታሮት በሽታ ሙሉ በሙሉ ይድናል ወይስ አይድንም? በየትኛውም ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታ በጊዜውና በአግባቡ ከታከመ ሙሉ በሙሉ እንደሚድን ዶክተር ቤተልሔም አረጋግጠዋል። በተለይም አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታን ሰዎች እቤታቸው በሚያደርጉት ትሪትመንት (የአኗኗርና አመጋገብ ዘይቤያቸውን በማስተካከል) ሊያድኑት እንደሚችሉም አመላክተዋል። በተጨማሪም ወደ ሕክምና ተቋም ቢሄዱ፤ የሰገራ ማለስለሻ፣ ፊንጢጣ ላይ የሚቀባ የህመምና ዕብጠት መቀነሻ መድኃኒት እንደሚሰጥ በመግለጽ ይህ ከተስተካከለ የአኗኗር ዘይቤያቸው ብሎም በብዛት ውኃ ከመጠጣት ጋር ሲሠናሰል በመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ኪንታሮት የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህንን አልፎ ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ላይ ቢደርስ እንኳን የተለያዩ የቀዶ ሕክምና አማራጮች እንዳሉ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት እንደ ኪንታሮቱ መጠን ‘ረበርባንድ’ (ዕባጩን ዙሪያውን በመቋጠር በጊዜ ሂደት ደርቆ እንዲረግፍ የማድረግ ሕክምና) እና ኪንታሮቱን (የደም ሥሮቹን ዕባጭ) በቀጥታ በቀዶ ሕክምና በማውጣት ማከም ይቻላል፤ መዳንም ይቻላል ብለዋል። · ኪንታሮት እና ባሕላዊ ሕክምና ከላይ እንደገለጽነው (የኑሮ ዘይቤን ማስተካከል፣ ውኃ በብዛት መጠጣት፣ በፋይበር የበለጸጉ ምግቦችን ማዘውተር፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ) ከዚያም ዘመናዊ ሕክምና መከታተል ተገቢ መሆኑን የሕክምና ባለሙያዋ መክረዋል። በአንጻሩ በባሕል (በልማድ) ፊንጢጣ ውስጥ የሆነ ነገር መቅበር፣ ኪንታሮትን በግለት መተኮስ ለካፋ ችግር ሊያጋልጥ ስለሚችል ይህን ከማድረግ መቆጠብ ይመከራል ብለዋል። ምክንያቱም ለፊንጢጣ መጥበብ (በሚጸዳዱበት ጊዜ ለመሰንጠቅና መድማት) ብሎም ለመሰል የጎንዮሽ ጉዳቶች ሊዳርግ እንደሚችል አስረድተዋል። ኪንታሮት በአግባቡ በቀዶ ሕክምና ካልወጣ በባሕል (ልማድ) መነካካቱ ለባክቴሪያ እንደሚያጋልጥ፤ ባክቴሪያው ደግሞ ከፊንጢጣ አልፎ ወደ ሌሎች የሰውነት ክፍሎች (ለምሳሌ ወደ ታፋና አካባቢው) የሚዛመት መግል የያዘ ከፍተኛ ኢንፌክሽን ያጋልጣል ብለዋል። በዚህ ጊዜ ወደ ሕክምና ሲመጡ ሕክምናውን በጣም ከባድ (ውስብስብና አስቸጋሪ) ያደርገዋል ነው ያሉት። · የፊንጢጣ ካንሰርና የኪንታሮት በሽታ ቀደም ብለን እንዳነሳነው የኪንታሮት በሽታ ምልክቶች፤ ማሳከክ፣ ዕባጭ፣ መድማት እና ህመም ናቸው ያሉት ዶክተር ቤተልሔም፤ የፊንጢጣ ካንሰርም ተመሳሳይ ምልክቶች ይኖሩታል ይላሉ። ስለዚህ ማንኛውም ሰው በፊንጢጣ በኩል ደም ሲመለከት ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም እንዲሄድ መክረዋል። ምክንያቱም ይላሉ፤ በፊንጢጣ በኩል ደም የሚታየው አንድም በኪንታሮት በሽታ እንዲሁም በአንጀት ቁስለት፣ በፊንጢጣ ካንሰር፣ በጨጓራ ቁስለት እና በትልቁ አንጀት ካንሰር ምክንያት ሊሆን ስለሚችል ነው። ከመድማት በተጨማሪ የፊንጢጣ ቁስለት በስፋት ከታየ ካንሰር ሊሆን እንደሚችልም አመላክተዋል። ቁስለቱ ፊንጢጣ ውስጥ ስለሚሆን በእጅ መንካትና ማወቅ የማይቻልበት ሁኔታ እንደሚኖርም ጠቁመዋል። · ምክረ ሐሳብ ለኪንታሮት በሽታ ላለመጋለጥ ወይም ከመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ወደ ቀጣዮቹ ደረጃዎች እንዳይሸጋገር መንስዔዎቹን መቀልበስ ተገቢ መሆኑን በአጽንዖት አንስተዋል። በዚህም መሠረት ድርቀት እንዳይኖር ማድረግ ቀዳሚው መፍትሔ መሆኑን አስገንዝበዋል። ለዚህም በቂ ውኃ መጠጣት፣ ከ25 እስከ 30 ግራም ፋይበር በየቀኑ መውሰድ (በደንብ ፋይበር ያላቸው ምግቦችን መመገብ ለምሳሌ፡- ጎመን፣ ቆስጣ፣ ብርቱካን፣ ሙዝ፣ አፕል፣ ባቄላ፣ ገብስ፣ አጃ፣ ስንዴ) ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም ድርቀትን ለመከላከል ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባ በመግለጽ፤ በሥራ ባሕርያቸው ቢሮ ውስጥም ሆነ ሌላ ቦታ መቀመጥ የሚያበዙ ሰዎች በመሐል በመነሳት መንቀሳቀስ እንዲሁም ከሥራ ሲወጡ በእግር መሄድ (ዎክ ማድረግ) እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ማድረግ ለአንጀት እንቅስቃሴ ዕገዛ በማድረግ ድርቀት እንዳይኖር ይጠቅማቸዋል ብለዋል። ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያለባቸው ሰዎችም ክብደታቸውን እንዲቀንሱ መክረው፤ ይህ ሲሆን ከፊንጢጣ ውጭ የነበረው የደም ሥር ዕብጠት (የኪንታሮት በሽታ) ወደ ነባር ቦታው እንዲመለስ ወይም ባለበት እንዲቆይ (በይበልጥ ተገፍቶ እንዳይወጣ) ይረዳል ይላሉ። ከልማዳዊ ሕክምና በመራቅ ዘመናዊ ሕክምናን ቀዳሚ ምርጫ ለማድረግ በተለይም ቀድሞ መከላከል የሚቻልበትን ብልኀት ለማዳበር ስለ ኪንታሮት በሽታ በስፋት ግንዛቤ መፍጠር ተገቢ ነው ይላሉ። በፊንጢጣ በኩል ደም ሲታይ ሁሌም ኪንታሮት ላይሆን እንደሚችልና ካንሰር ሊሆን እንደሚችልም በመገንዘብ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ ወደ ሌሎች ደረጃዎች ሳይሸጋገር በማከም እንዲድን ማድረግ ተገቢ መሆኑን መክረዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የኢትዮጵያ የማከናወን አቅም የተገለጠበት
Jun 23, 2026 1992
በኢዜአ ዐይን…! በዮሐንስ ደርበው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጥቅም ንጥልም ቀላልም አይደለም፤ በተለያዩ ዐውዶች ገዝፎ ይገለጣል እንጅ። ለአብነትም፤ የደን ሽፋንን በማሳደግ የዓየር ንብረት ተጽዕኖን በመቀነስ ብሎም በመከላከል፣ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ እንዲሁም በመከላከል ምርታማነትን በመጨመር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የከተማ ውበት መጠበቅን ጨምሮ የተለያዩ ጥቅሞችን በቀጥታ ለሰው ልጆች ይቸራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ አረንጓዴ ዐሻራ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልጽግና አሠናሥሎ የሚያረጋግጥ ብሔራዊ ኢኒሼቲቭ ነው። የደን፣ የሰብልና ሁለንተናዊ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ወሳኝ የልማት አቅጣጫም ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት ጽንሰ ሐሳቡ ከችግኝ ተከላ የተሻገረው አረጓዴ ዐሻራ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ መነሻ፤ የተራቆተ አካባቢን ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ከማድረግ የላቀ ድርብርብ ግብ ያለው ሰፊ መርሐ-ግብር ነው። በዚህም መሠረት፤ እንደየ ሥነ-ምኅዳሩ የሚላመዱ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ላላቸው ችግኞች፣ ለደን ሽፋን ማደግ የጎላ ሚና ለሚኖራቸው ችግኞች፣ ለከተማ ውበትና ለማረፊያ ጥላ ለሚሆኑ ዛፎች፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የሚችሉ ዛፎች የሚተከሉበት ነው። ይህም አንድን አካባቢ አረንጓዴ ከማድረግ ልቆ በረሃማነትንና የዓየር ንብረት ተጽዕኖን በመቀነስ፣ ምርታማነትን በመጨመር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በማሳደግ በቀጥታ ሕብረተሰቡን የሚጠቅም ትልቅ ኢኒሼቲቭ መሆኑን ያስረዳል። የተለያዩ ክፍላተ-ዓለማት አንድም በካፋ ቅዝቃዜ እንዲሁም መደበኛ የኑሮ ሁኔታን በሚያናጋ አደገኛ ሙቀት ብሎም በድንገተኛ ጎርፍ እና ሰደድ እሳት በሚታመሱበት ጊዜ፤ እነዚህንና መሰል ችግሮችን ቀድሞ ለማረቅ አንዱ መፍትሔ አረንጓዴ ዐሻራን በስፋት ማከናወን መሆኑ ይታመናል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነትና ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባለፉት ዓመታት በብርቱዎቹ ኢትዮጵያውያን ርብርብ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል፤ ውጤቱንም ሕዝቡ ዐይቷል። ከውጤቶቹ መከካልም ለአብነት፤ ከሀገራዊ ለውጡ በፊት 17 ነጥብ 2 በመቶ የነበረው የደን ሽፋን አሁን ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማደጉ፣ የምርታማነትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት መጨመር ብሎም ውብና አረንጓዴ ከተሞች መስፋፋት የሚሉት ይነሳሉ። በሕዝቡ ዘንድ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ተፈጥሮን የመንከባከብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጉዳይ ጭምር ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል። የአረንጓዴ ዐሻራን ውጤት ላጣጣመ ሥራውን በንቃት እንዲከውን መካሪ ባያሻም፤ ካለፈው የበለጠ ውጤት እንዲገኝ ዛሬ ላይ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚነታቸውን በሚያረጋግጠው የአረንጓዴ ዐሻራ በነቂስ መሳተፍ እና ባሕላቸው ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ከአረንጓዴ ዐሻራ ትሩፋቶች መካከል • በሰብል፣ ፍራፍሬ፣ ቡና ምርታማነት እና በሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን ያደረገው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አሁን ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ነው። ከበርካታ ትሩፋቶቹ መካከልም የምርታማነት ማደግ ተጠቃሽ ነው። ይህን ተከትሎም የሕብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አድጓል። ይህን ሐሳብ በአኃዝ አስደግፎ ብናየው፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፊት (በ2010 ዓ.ም) በሔክታር የሚመረተው ስንዴ 22 ኩንታል፣ በቆሎ 30 ኩንታል፣ ጤፍ 17 ኩንታል እንዲሁም ገብስ 23 ኩንታል ነበር። ከኢንሼቲቩ ትግበራ በኋላ ደግሞ (በ2017 ዓ.ም) ስንዴ በሔክታር 36 ኩንታል፣ በቆሎ 46 ኩንታል፣ ጤፍ 20 ኩንታል፣ ገብስ 30 ኩንታል ማምረት ተችሏል። በዚህም መሠረት በ2017 ዓ.ም 7 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር መሬት በስንዴ ሰብል በመሸፈን 280 ሚሊየን ኩንታል ማምረት ተችሏል። ስንዴን በትጋት በማምረትም ከውጭ ለማስገባት ይወጣ የነበረን 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል። በሌላ በኩል ደግሞ፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፍራፍሬው ዘርፍ ዕድገትም ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል። በዚህም ገበያውን ከማረጋጋት ባለፈ ሕብረተሰቡ (አምራቹ) ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ በዚያው ልክ እንዲያድግ አስችሏል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ አቮካዶን በቀዳሚነት ወደ ውጭ የምትልክ ሁለተኛዋ ሀገር እንድትሆን አስችሏታል። ሌላኛው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትሩፋት የቡና ልማት መስፋፋትና የውጭ ምንዛሬ ማደግ ነው። ይህን በአሥረጂ አስደግፈን ብንመለከት፤ በ2011 ዓ.ም በ600 ሺህ ሔክታር ላይ ቡና ተተክሏል። 500 ሺህ ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 738 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኝቷል። እንዲሁም በ2017 ዓ.ም 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ቡና ተተክሏል። 1 ነጥብ 58 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 2 ነጥብ 65 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢም ማግኘት ተችሏል። እንዲሁም ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጋር በተያያዘ ለ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። ከላይ የተጠቀሱ ማሳያዎችን (ናሙናዎችን) ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በቀጥታ ለሕዝቡ ጥቅም የቆመ መርሐ-ግብር መሆኑን መገንዘብ አያዳግትም። ስለዚህ በቀጣይ ሕብረተሰቡ በዚህ ኢኒሼቲቭ ላይ ያለጠባቂነት በንቃት በመሳተፍ እና ባሕሉ በማድረግ ተጠቃሚነቱንም በዚያው ልክ ለማሳደግ መትጋት ይጠበቅበታል። እስከ ዓለም ከፍታ ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር የሚዳርገው ህመም ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አበርክቶዎች መካከል • በመሬት መራቆት መቀነስ፣ በደን ሽፋን ማደግ፣ በውኃማ አካላት መስፋፋት ረገድ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ፤ የአካባቢ መራቆትን በመቀነስና በመቅረፍ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል፣ በደን መጨፍጨፍ ምክንያት ይከሰት የነበረን የበረሃማነት መስፋፋት ቀንሷል፣ የደን ሽፋንን ጨምሯል፣ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ መሬት እንዲያገግም በማድረግ ምርታማነትን ጨምሯል። በተጨማሪም የውኃማ አካላትን መመናመን ቀንሷል (ደርቀው የነበሩ ስፍራዎች ወደ ቀድሞ ውኃማ ይዘታቸው እንዲመለሱ አስችሏል)፣ የአካባቢ መራቆትና የዓየር ንብረት ፈተናዎችን በመቀነስ ረገድም የራሱን ከፍተኛ ሚና አበርክቷል። ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትግበራዋ ስኬታማነት ዓለም ዕውቅና ችሯታል በሀገር አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማትና መሪዎች ዘንድ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ትግበራ ተወድሷል። ከእነዚህ ዕውቅናዎች መካከል፤ የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአግሪኮል ሽልማት መስጠቱ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) Outstanding African Leadership Award ማግኘታቸው የሚሉት ይጠቀሳሉ። እንዲሁም፤ ኢትዮጵያ 2ኛውን የአፍሪካ የዓየር ንብረት ጉባዔ ተመርጣ ማስተናገዷ፣ ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት የሥርዓተ-ምግብ ጉባዔ ማስተናገዷ፣ በ80ኛው የዓለም ምግብና እርሻ ድርጅት ጉባዔ ለዘላቂ ደን ልማት የተሰጣት ዕውቅና እንዲሁም ኢትዮጵያ ኮፕ-32 (COP- 32) ለማስተናገድ መመረጧ በዘርፉ ላከናወነችው አርዓያነት ያለው ተግባር የተሰጡ ዕውቅናዎች ናቸው። ኢትዮጵያ ስኬታማውን የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትልሟን ለሀገራት ማጋራቷ ኢትዮጵያ በራሷ ሐሳብ አመንጭነት ሕዝቧን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እየተሰጠ ባለ ያልተቆራረጠ ጠንካራ አመራር በአረንጓዴ ዐሻራ ዘርፍ ያስመዘገበችውን ስኬት፣ አሠራር (ልምድ) እና ችግኝ ለተለያዩ ሀገራት አጋርታለች። ይህም እየሄድችበት ያለው መንገድ ሁሉ ተባብሮ ማደግን ያነገበ ለመሆኑ አሥረጂ ነው። በዚህም መሠረት፤ በ2012 ዓ.ም ለፑንትላንድ፣ በ2012 ዓ.ም ለፓኪስታን፣ በ2012 ዓ.ም ለጂቡቲ፣ በ2013 ዓ.ም ለደቡብ ሱዳን፣ በ2013 ዓ.ም ለሩዋንዳ እና ለሌሎችም በዘርፉ ያላትን የተመሠገነ ልምድ አጋርታለች። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ የተመራበት ሂደት የኢኒሼቲቩ ሐሳብ አመንጭ እና አመራር ሰጭ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ናቸው። ወደ ክልል፣ ዞን ወረዳ እና ቀበሌ በማውረድም በተቀናጀ ትጋት በመመራቱም ስኬታማ መሆን ችሏል። በዚህም መሠረት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነትና አመራር ሰጭነት፣ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እና ባለድርሻ አካላት ቅንጅት፣ በክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮችና ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ቅንጅት፣ በየደረጃው በተዋቀረ የቴክኒክ ኮሚቴ አማካኝነት፣ በተደራጀ የሕዝብ ተሳትፎ አማካኝነት የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በስኬት እየተተገበረ ይገኛል። ከአረንጓዴ ዐሻራ ጋር በተያያዘዘ የቀጣይ አቅጣጫዎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ የለውጡ መንግሥት ከመጣ ወዲህ ላለፉት ዓመታት በተቀናጀ አግባብ ተመርቷል፤ አሁንም እየተተገበረ ነው። በቀጣይ ደግሞ ኢኒሼቲቩ እንዴት መከናወን እንዳለበት ግቦች ተቀምጠዋል። በዚህም መሠረት፤ የሕዝብ ባለቤትነትን አጠናክሮ ማስቀጠል (አረንጓዴ ባሕል መገንባት)፣ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎችን ማስፋትና በደን ላይ የሚደርሰውን ጫና መቀነስ፣ የሕግና የፖሊሲ ማሻሻያ የሚፈልጉ ጉዳዮችን ለይቶ በጥናት መመለስ የሚሉት የቀጣይ አቅጣጫዎች ናቸው። በተጨማሪም፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ የሚገኘውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት አጠናክሮ ማስቀጠል፣ የባለድርሻ አካላት እና የተቋማት ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር፣ በክረምት ወራት የሚተከሉ ችግኞችን በበጋ ወራት በአግባቡ መንከባከብ ከቀጣይ አቅጣጫዎች መካከል ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በቢሾፍቱ ማስጀመራቸው ይታወቃል። በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክትም፤ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በሆኑበት በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ወቅት አረንጓዴ ለሆነች ነገ፣ ሁላችንም ተስፋን እንትከል ሲሉ ለሀገሬው ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2011 ዓ.ም መጀመሩም የሚታወስ ነው። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #ተስፋን_እንትከል
ትንታኔዎች
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 2187
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው  
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 4052
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ።   ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…! 
Jun 15, 2026 2469
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 7813
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 3591
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 17095
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 10165
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 15925
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 89008
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 69308
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 49537
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 47092
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 35172
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 34670
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 34131
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 33340
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 89008
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 69308
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 49537
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 47092
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 340
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ልዕልና በአረንጓዴው ከፍታ
Jun 25, 2026 1142
(በዮርዳኖስ ዓባይነህ) የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ለማልማት የጀመረችው ታሪካዊና አርአያነት ያለው ብሔራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ዘመቻ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ አዋቂዎችና ልዩ ልዩ ተቋማት በነቂስ በመውጣት በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በከፍተኛ የሕዝብ ንቅናቄና በአንድነት መንፈስ ለመትከል ችለዋል። በዚህ ተከታታይ የችግኝ ተከላና እንክብካቤ ሥራ ምክንያት ለዓመታት ተራቁተው የነበሩ ተራራማና ኮረብታማ ቦታዎች እንዲሁም የሀገሪቱ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያገግም ሆኗል፤ ይህም የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ የከርሰ-ምድር ውሃ መጠን እንዲጨምር ተጨባጭ አስተዋጽኦ አበርክቷል። አካባቢን ከመጠበቅ ባሻገር፣ መርሃ-ግብሩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የፍራፍሬ፣ የቡናና የቅመማ ቅመም ችግኞችን በማካተት አርሶ አደሩ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝና የምግብ ዋስትናው እንዲረጋገጥ ትልቅ የኢኮኖሚ በር ከፍቷል። በተጨማሪም በዋና ዋና ከተሞች የተገነቡት ውብ አረንጓዴ ፓርኮች ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ንጹህና ማራኪ ከማድረጋቸውም በላይ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ እየሆኑ ይገኛሉ። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ለአሁኑ ትውልድ የኢኮኖሚ ዋስትናን፣ ለወደፊቱ ደግሞ የተስተካከለ የአየር ንብረትና ለምለም ሀገርን የሚያስረክብ ታላቅ የትውልድ ቅርስ በመሆኑ፣ የተተከሉትን ችግኞች ተንከባክቦ ማሳደግና ዘላቂነታቸውን ማረጋገጥ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ነው። 👉ከተፈጥሮ ጋር የተጻረረው የሰው ልጅ ስልጣኔ የሰው ልጅ በምድር ላይ መኖር ከጀመረበት ጥንታዊ ዘመን አንስቶ በሕይወት ለመቀጠልና ሕልውናውን ለማረጋገጥ ከተፈጥሮ ብሎም ከመሰሎቹ ጋር ጠንካራ እና ቀጣይነት ያለው መስተጋብር ሲያደርግ ቆይቷል። ነገር ግን ይህ መስተጋብር ሚዛኑን እየሳተ መጥቶ፣ ከጥንቱ የግብርና ስልጣኔ እስከ ዛሬው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ድረስ በሰው ልጅ እጅ የተፈጸመው የተፈጥሮ መራቆት በምድር ላይ ከባድ ጠባሳ ጥሏል። የደን መጨፍጨፍ፣ የአፈር መሸርሸር እና የውሃ አካላት መናመን የዚሁ አውዳሚ ጉዞ ውጤቶች ናቸው። አግባብ ያለው የአካባቢ ጥበቃ ባለመደረጉም፣ በቢሊዮን የሚቆጠሩ አዕዋፋትና የዱር እንስሳት ለዘመናት ከኖሩበትና ለነሱ ከሚስማማቸው ቀያቸው ለመሰደድ ተገድደዋል። የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና ግብርና ድርጅት (FAO) በ2016 እ.ኤ.አ ባወጣው ጥናት መሠረት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ 92 ሺህ ሄክታር ደን ይጨፈጨፋል። ለዚህም የእርሻ መሬት ማስፋፋትና የማገዶ ፍላጎት መጨመር በዋና ምክንያትነት ይጠቀሳሉ። ይህ የዓለም አቀፍ ስጋት ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ደግሞ የራቀ ሳይሆን የውስጥ ቁስል ነበር። በደን መጨፍጨፍና በአፈር መሸርሸር ምክንያት በተደጋጋሚ የተከሰቱት የድርቅ፣ የረሃብ፣ የመሬት መንሸራተት እና የሕዝቦች መፈናቀል ታሪኮች የቅርብ ጊዜ ትዝታዎቻችን ናቸው። 👉የ"ክፉ ቀን" ትርክት እና የስነ-ልቦና ጠባሳ ከ1888 እስከ 1892 እ.ኤ.አ በሀገራችን የተከሰተውና '’ክፉ ቀን'’ ተብሎ የሚታወቀው አሰቃቂ የረሃብ ታሪክ ፣ ከዚያም በኋላ በወሎና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የታዩት ድርቆች በዓለም መገናኛ ብዙሃን ጎልተው ሲዘገቡ ቆይተዋል። ይህ አሳዛኝ ክስተት ለውጭ መገናኛ ብዙሃንና ተቋማት ተጨማሪ ዝና እና ገቢ ማግኛ ሰበብ ሲሆን፣ ለሕዝባችን ግን ለዘመናት ያልተሻረ የስነ-ልቦና ቁስል ጥሎ አልፏል። ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ የድህነት እና የረሃብ ተምሳሌት አድርጎ በመሳል፣ ኢትዮጵያውያንን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን አንገት ያስደፋ ጥቁር ታሪክ ሆኖ ኖሯል። ታዲያ ይህንን የውርደት ትርክት የሚቀይር፣ ሀገራዊ ክብርን የሚመልስና ቀጣይነት ያለው የአካባቢ ጥበቃን የሚያረጋግጥ ወሳኝ እርምጃ መውሰድ የህልውና ጉዳይ ነበር። 👉አረንጓዴ አሻራ፦ ተግዳሮቶችን የመለወጥ የፅናት ጉዞ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት፣ በተቋማት ቅንጅትና በተደራጀ የሕዝብ ንቅናቄ "የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር" ተጀመረ። በመጀመሪያው ዓመት “40 ዛፎች በነፍስ ወከፍ” በሚል መሪ ሃሳብ የተጀመረው ዘመቻ፣ ከዕቅድ በላይ 18 በመቶ ስኬት በማስመዝገብ የሕዝቡን የልማት ጥም አሳየ። በሁለተኛው ዓመት (2012 ዓ.ም) ዓለምን ያሸበረው የኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ወረርሽኝ ቢከሰትና ማኅበራዊ መራራቅ፣ ጥንቃቄዎች እንዲሁም ከቤት ሆኖ መሥራት ግዴታ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያውያን የአረንጓዴ ጉዞ አልተገታም። “እየተጠነቀቅን እንተክላለን” በሚል መሪ ሐሳብ ፣ ማኅበረሰቡ ደህንነቱን ጠብቆ በመንቀሳቀሱ ከዕቅድ በላይ 14 በመቶ ችግኝ መትከል ተችሏል። 👉የሰባት ዓመታት ስኬቶች በቁጥር እና የስነ-ምህዳር መነቃቃት ይህ ስራ ለአንድና ለሁለት ዓመት የተደረገ ዘመቻ ሳይሆን የሰባት ዓመታት ተከታታይ የፅናት ጉዞ ነበር። ከ2011 እስከ 2017 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በኢትዮጵያ ምድር ላይ ተተክለዋል። የችግኞቹ የስብጥር ይዘትም ስልታዊ የደን ልማትን ያሳያል፦ 60 በመቶ የጥምር እርሻ ደን (Agroforestry) 35 በመቶ የተፈጥሮ ደን ሽፋን 5 በመቶ የከተማ ውበት ዛፎች ከተከናወኑት የክትትልና ቁጥጥር ሪፖርቶች መረዳት እንደሚቻለው፣ ከተተከሉት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥ በአማካይ ከ75 በመቶ እስከ 80 በመቶ በላይ የመፅደቅ መጠን (Survival Rate) ማሳየት መቻላቸው የሥራውን ውጤታማነት በተጨባጭ ያረጋግጣል። ይህ መጠነ-ሰፊ ስራ ቀደም ሲል ከ2010 እስከ 2016 ዓ.ም ይከሰት የነበረውን የደን መጨፍጨፍ በ65 ሺህ ሄክታር በመቀነስ፣ የሀገሪቱን የደን ሽፋን በ11 ነጥብ 4 በመቶ ከፍ እንዲል አድርጓል። የተከናወነው የተቀናጀ የልማት ስራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስና የውሃ አካላትን በማንሰራራት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ይህ የደን ሽፋን ዕድገት ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከካርቦን ሽያጭ (Carbon Trading) እና ከአየር ንብረት አረንጓዴ ፋይናንስ (Green Finance) ልታገኝ የምትችለውን የኢኮኖሚ ዕድል በከፍተኛ ደረጃ የሚያሰፋላት ነው። 👉ከስነ-ምህዳር ጥበቃ ወደ ቢሊዮን ዶላር ኢኮኖሚ ግንባታ እና የኮሪደር ልማት የአረንጓዴ አሻራ ስኬት ስነ-ምህዳሩን በማደስ ብቻ አልተገደበም፤ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንትም ጭምር ቀይሯል። መሬትን የማከምና የአፈር እርጥበትን የመመለስ ስራው በ2017 ዓ.ም 280 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ በሀገር ውስጥ ለማምረት አስችሏል። ይህ ውጤት ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ለስንዴ ማስመጫ ታወጣ የነበረውን አንድ ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ያስቻለ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው። በተጨማሪም ይህ አረንጓዴ ልማት ኢትዮጵያን በአፍሪካ 2ኛዋ የአቮካዶ ምርት ላኪ ሀገር ያደረጋት ሲሆን፣ በ2017 ዓ.ም የቡና ምርትን በማስፋፋትና ጥራትን በመጨመር 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ታሪካዊ የውጭ ምንዛሪ ለማስመዝገብ አስችሏል። ይህ ታላቅ ስኬት የተገኘው የኢኮ-ሲስተም ልማትን፣ የገጠር ልማትን፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትን እና የከተማ ኮሪደር ልማትን (Urban Corridor Integration) ባካተተ የተቀናጀ ስትራቴጂ ነው። በተለይም በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ከመቀየር ባለፈ፣ ለነዋሪዎች ምቹና ሰፊ የእግር መንገዶችን፣ ማራኪ የአረንጓዴ ስፍራዎችንና መናፈሻዎችን በመፍጠር ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች ደህንነቱ የተጠበቀና ማራኪ የከተማ ቱሪዝም (Eco-tourism) መዳረሻዎችን በተግባር መፍጠር ችሏል። 👉የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ መሪነት እና ዓለም አቀፍ እውቅና ይህ ንቅናቄ በሀገር ውስጥ ካለው ፋይዳ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ "የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ" መሪ እንድትሆን አድርጓታል። እንደ ኤርትራ፣ ጅቡቲ፣ ፓኪስታን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሩዋንዳ ያሉ ሀገራት ከኢትዮጵያ ተሞክሮ በመቅሰም በሀገራቸው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር መጀመራቸው የዚህ ማሳያ ነው። በተጨማሪም የዓለም ምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"አግሪፎድ ሻምፒዮን" እና "የላቀ የአፍሪካ አመራር ሽልማት" መስጠቱ ፣ ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ምግብ ጉባኤን ማስተናገዷ እና በ80ኛው የፋኦ ጉባኤ ላይ ለሀገሪቱ አጠቃላይ ዕድገት የተሰጠው እውቅና የዓለምን አድናቆት ያረጋገጡ ክስተቶች ናቸው። እነዚህ ዓለም አቀፍ ምስክርነቶች ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ተስሎባት የነበረውን የድርቅ እና የረሃብ አፍራሽ ትርክት በአረንጓዴ ልማት፣ በአንድነት እና በምርታማነት በተግባር የቀለበሰችበት ታላቅ ድል ነው። 👉ስምንተኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ፡ "ተስፋን እንትከል!" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ማስጀመራቸው ይታወቃል። መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልፅግና አሰናስሎ የሚያረጋግጥ ብሔራዊ የልማት አቅጣጫ መሆኑ ተመስክሮለታል። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ዘመቻ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ መጀመሩ ጥልቅ ትርጉም አለው። ተስፋ የነገን ብሩህ ምዕራፍ ዛሬ ላይ ለመጻፍ የሚያስችል አረንጓዴ መቀነት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉትም፤ አረንጓዴ ዐሻራ አፈራችንን ከስደት፣ የታላቁን ህዳሴ ግድባችንን ደግሞ ከደለል የሚታደግ ብሔራዊ ጋሻ ሆኗል። የአባቶቻችን የዓድዋ ድል ወራሪን ያሳፈረ ታላቅ ገድል እንደነበረ ሁሉ፣ የአሁኑ ትውልድ በአረንጓዴ ዐሻራ እያከናወነ ያለው ተግባርም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አዲስ የታሪክ ገድል እየሆነ ይገኛል። ይህ ንቅናቄ የሀገሪቱን የተረጂነት ታሪክ ወደ ማድረግና ራስን ወደ መቻል ዘመን የሚያሸጋግር የመደመር መርህ መገለጫ ነው። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ ቁጥራዊ መረጃዎች የህዝብ ቁርጠኝነት ማሳያ ናቸው። ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል። በዘንድሮው መርሃ ግብር ደግሞ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን፤ ይህም አጠቃላይ የተተከሉትን ችግኞች ቁጥር ወደ 56 ቢሊየን ያደርሰዋል። ይህ ታላቅ ስኬት እዚህ ላይ አያበቃም፤ ሀገሪቱ በፈረንጆቹ 2029 የሚካሄደውን የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) ስታስተናግድ፣ በአጠቃላይ 65 ቢሊየን ችግኞችን መትከል የቻለች መሪ ሀገር መሆኗን ለዓለም የምታበስርበት ታሪካዊ ምዕራፍ ይሆናል። በክረምቱ ወራት እያንዳንዱ ዜጋ "ተስፋን በመትከል" የዓድዋን የኩራት ስሜት በአረንጓዴ ልማት ሊደግመው ይገባል። የበለፀገችና የተከበረች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ፣ የተተከሉትን ችግኞች ተንከባክቦ ማሳደግና የአረንጓዴ ዐሻራን ስኬት ማስፋትና ማስቀጠል የዛሬው ትውልድ የማይታጠፍ ብሔራዊ ጥሪ ነው። 👉የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች በኢትዮጵያ እስከአሁን የተመዘገቡ ስኬቶችን ዘላቂ ለማድረግና የተፈጥሮ ቅርሶቻችንን ይበልጥ ለማጠናከር የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎች በግልጽ ተቀምጠዋል። መንግሥት የልማቱን የሕዝብ ባለቤትነት ማረጋገጥና ማቀናጀት፣ አረንጓዴ ልማትን እንደ ባህል መገንባት፣ የቴክኖሎጂ እሴቶችን በመጠቀም የሥራ ዕድሎችን ማስፋፋት፣ በተፈጥሮ ሀብት ላይ የሚደረገውን ጫና መቀነስ፣ እንዲሁም አዲስ የተገነቡ የኮሪደር ልማቶችንና ፓርኮችን በመጠበቅ የጎብኝዎችን ደህንነት ማረጋገጥና የተፈጥሮ ቅርስን አብሮ ማጠናከር ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጧል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም