ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ የሚሳተፉ ልዑካን አዲስ አበባ መግባት ጀመሩ
Jul 26, 2026 65
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦በ49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ለመሳተፍ የአፍሪካ ሀገራት ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በዚሁ መሠረት የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ዶክተር ኤድዋርድ ቢዚማና አዲስ አበባ ገብተዋል። አምባሳደር ዶክተር ኤድዋርድ ቢዚማና ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ሹም መላኩ በዳዳ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። 49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ከሐምሌ 21 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል። በጉባኤው ለመሳተፍ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች እና የልዑካን ቡድን አባላትም አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያ በአይነቱ ለየት ያለ የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን ሲምፖዚየም ታስተናግዳለች
Jul 26, 2026 60
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ከፍተኛ ትኩረት የሚስብ የ2026 የአፍሪካ ሎጂስቲክስና ኮሙኒኬሽን ሲምፖዚየም (African Logistics and Communication Symposium) ከሃምሌ 20 እስከ 25 ቀን በአዲስ አበባ ታስተናግዳለች። በሲምፖዚየሙ 40 ሀገራትና 26 ዋና ዋና አለም አቀፍ የኢንዱስትሪ አጋሮች ይሳተፉበታል ተብሎ ይጠበቃል። ዝግጅቱን በማስመልከት የመከላከያ የውጭ ግንኙነት እና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክትሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ እና በአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ (አፍሪኮም) የሎጂስቲክስ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀነራል ፓል ፍሪክና ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የመከላከያ የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ፤በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ሎጂስቲክስና ኮሙኒዩኬሽን ሲምፖዚየም ኢትዮጵያ ለዚህ ታላቅ አህጉራዊ መድረክ አስተናጋጅ ሆና መመረጧ በቀጠናው ለሰላም ያበረከተችው አስተዋፅኦ፣ በመንግሥት የተመዘገበው የልማት ውጤት፣ የአዲስ አበባ ከተማ እያሳየች ያለው ፈጣን እድገት እና ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን የማስተናገድ አቅሟ የፈጠረው ውጤት መሆኑንም ጠቁመዋል። ሲምፖዚየሙ በአሜሪካና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የትብብር ግንኙነት የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ በአፍሪካ የመከላከያ ተቋማት መካከል የልምድ ልውውጥና የጋራ ትብብር የሚያጎለብቱበት መድረክ መሆኑን አመልክተዋል። ሎጂስቲክስና ኮሙኒዩኬሽን በማንኛውም ወታደራዊም ሆነ ሰላማዊ ተልዕኮ ስኬት ውስጥ ወሳኝ ሚና ያላቸው ዘርፎች መሆናቸውን የገለፁት ዳይሬክተሩ ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ፣ የተሻሉ አሠራሮችን በመቅሰም እና ለወደፊት የሚያጋጥሙ የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን ችግሮች የጋራ መፍትሔ ለማፈላለግ ወሳኝ አጋጣሚ መሆኑን ጠቁመዋል። ከአጋር ሀገራት የሚገኙ ልምዶችና ዕውቀቶች ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅምን ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ገልጸው፣ እንደዚሁም ኢትዮጵያም ያላትን ልምድ ለአጋር ሀገራት በማካፈል በአህጉራዊ ሰላምና ደህንነት ዘርፍ ያላትን አስተዋፅኦ የበለጠ እንደምታጠናክር ገልጸዋል። የአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (AFRICOM) የሎጂስቲክስ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀነራል ፖል ፍሊክስ በበኩላቸው፥ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የ2026 የአፍሪካ ሎጂስቲክስና ኮሙኒዩኬሽን ሲምፖዚየምን በጋራ በማዘጋጀቷ ከፍተኛ ደስታና ክብር እንደሚሰማቸው ገልፀው፣ ለሲምፖዚየሙ መሳካት ኢትዮጵያ ያደረገችውን ዝግጅት አድንቀዋል። ኮንፍረንሱ በአሜሪካና በአፍሪካ መካከል በሎጂስቲክስና በኮሙኒዩኬሽን ዘርፍ ያለውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እንደሚሆንም ጠቁመዋል። በቀጣዮቹ ቀናት ተሳታፊ ሀገራት የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅሞቻቸውን በመገምገም፣ ያሉ ክፍተቶችንና ተግዳሮቶችን በጋራ በመለየት ዘላቂ መፍትሔዎችን ለማፍለቅ እንደሚሠሩም ገልጸዋል። ሲምፖዚየሙ በትብብር፣ በፈጠራና በጋራ ትምህርት የተሞላ ፍሬያማ ሳምንት እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልጸው፣ በጋራ በመሥራት ጠንካራ የትስስር መረቦችን በመገንባት የሀገራትን አቅም ከፍ ማድረግና ለበለጠ ደህንነትና ብልጽግና መሠረት መጣል እንደሚቻል ተናግረዋል። በመጨረሻም ኢትዮጵያ ለዚህ ዓይነት ታላቅ አህጉራዊ ጉባኤ አስተናጋጅ ሆና መመረጧ ለመከላከያና ለሀገሪቱ ትልቅ ክብር መሆኑን ገልጸው፣ ለዚህ ስኬት አስተዋፅኦ ላበረከቱ የመከላከያ አመራሮች፣ የመንግሥት ተቋማት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምስጋና ማቅረባቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
ሀገራዊ ምክክሩ የልጄም የነገ ተስፋ ጭምር የሚሰራበት ነው
Jul 26, 2026 82
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ የልጄም የነገ ተስፋ ጭምር የሚሰራበት በመሆኑ ጤናዬ በፈቀደው ልክ እስከመጨረሻው ተሳትፌ አላማዬን አሳካለሁ ሲሉ በምክክር ጉባዔው ላይ ልጅ የወለዱት ሁለተኛዋ እናት ሀዳ አልመሀዲ ገልጸዋል። እናት ሀዳ አልመሀዲ ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን ብሎም የልጆቻችንን የነገ ተስፋ ብሩህ የሚያደርግ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ምንም እንኳን ቀኔ የደረሰ ነብሰ ጡር ብሆንም ጉባኤው ላይ በመሳተፍ ሀላፊነቴን ልወጣ መጥቼ በዚህ ሂደት ላይ እያለሁ የልጅ እናት መሆን ችያለሁ ሲሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በተመረጡት አጀንዳዎች ላይ ተጠናክሮ እየተካሄደ ሲሆን በርካታ አስገራሚ ጉዳዮችም እየታዩበት ይገኛሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ አንዱ ደግሞ የእነ አቶ አብዱልወኪል ከማል እና ወይዘሮ ሀዳ አልመሀዲ ቤተሰብ ታሪክ ተጠቃሽ ነው፡፡ ባል አቶ አብዱልወኪል ከማል የብልጽግና ፓርቲ አባል ሲሆኑ ባለቤታቸው ወይዘሮ ሀዳ አልመሀዲ ደግሞ የተፎካካሪው የቤንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ ቤህነን ፓርቲ አመራር ናቸው፡፡ የግል የፖለቲካ አመለካከታቸውን በየግላቸው ይዘው የጋራ ትዳራቸውን የሚመሩት ጥንዶቹ ታዲያ ሚስት ወይዘሮ ሀዳ ፓርቲያቸውን ወክለው በምክክሩ እንዲሳተፉ በጋራ መግባባት ወስነዋል፡፡ ወይዘሮ ሀዳ አልመሀዲ በምክክሩ ሂደት ልጅ የወለዱ ሁለተኛዋ እናት ሲሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር ጋር በመሆን በኢትዮጵያዊ ባህል ወይዘሮ ሀዳን አራስ ጥሪ ይዘው መርቀዋቸዋል፡፡ ለወላዷ እናት ምክክሩ በሚካሄድበት አዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በሚገኘው ሆቴል ምቹ ማረፊያ እና አስፈላጊው እንክብካቤ እንዲደረግላቸውም ተደርጓል፡፡ እናት ሀዳም ታዲያ ከወሊድ ሂደቱ ጀምሮ እየተደረገልን ያለው እንክብካቤ ኢትዮጵያዊ መደጋግፍን በተግባር ያየንበት ነው ብለዋል፡፡ ምክክሩ የልጄም የነገ ተስፋ ጭምር የሚሰራበት በመሆኑ ጤናዬ በፈቀደው ልክ እስከመጨረሻው ተሳትፌ አላማዬን አሳካለሁ ሲሉም ገልጸዋል፡፡ አቶ አብዱልወኪል ከማል እና ወይዘሮ ሀዳ አልመሀዲ ልጃቸው የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ታሪካዊ ሁነት መገለጫ በመሆኑ ስሙን "ኮሚሽን" ሲሉ መሰየማቸውንም ገልጸዋል፡፡
የገጠር ሞዴል መንደር አርሶአደሩ ዘመናዊ ሕይወት እንዲመራ አስችሎታል
Jul 26, 2026 144
ቦንጋ ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ የገጠር ሞዴል መንደር አርሶአደሩ ዘመናዊ ሕይወት እንዲመራ አስችሎታል ሲሉ የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር ዙሪያ ጨታ ቀበሌ የተገነባውን የባቾ ገጠር ሞዴል መንደር መርቀው ለተጠቃሚዎች አስረክበዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለፁት፣ ሞዴል የገጠር መንደሩ ለሰውና ለእንስሳት ምቹ መኖሪያን የሚፈጥር፣ የማር፣ የዓሳና ሌሎችም የልማት ስራዎችን ያካተተ ነው ብለዋል። የገጠር ሞዴል መንደሮቹ የሌማት ትሩፋት ስራዎችን ውጤታማ በማድረግ የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ አቅም ለማሳደግ እንደሚያግዙም ተናግረዋል። ዛሬ የተመረቀው የባቾ ሞዴል የገጠር መንደር ይህን ለማሳካት የሚያስችል በመሆኑ ልምዱን ማስፋት ላይ እንደሚሰራ አንስተዋል። የገጠር ሞዴል መንደሩ የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ ናቸው። ባቾ ገጠር ሞዴል መንደር የሌማት ትሩፋትና ዘመናዊ አገልግሎቶችን ያሟላ መሆኑ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ስርዓት የሚቀይር ነው ብለዋል። የአመያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ደጀኔ በበኩላቸው፤ ትኩረት ተነፍጎት የቆየውን የገጠሩ ማህበረሰብ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የገጠር ሞዴል መንደር ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል። የገጠር ሞዴል መንደሩ የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭንና የሶላር፣ የንፁህ የመጠጥ ውሃ እና ሌሎች አገልግሎቶችንም ያካተተ መሆኑን ገልፀዋል። ከግንባታው ተጠቃሚዎች መካከል አቶ ታምሩ ተፈራ እና አቶ ተፈራ ሳካሎ፤ የገጠር ሞዴል መንደሩ ሁሉንም አገልግሎቶች ያሟላ በመሆኑ ዘመናዊ ሕይወት መምራት ያስችለናል ብለዋል። ይህም የገጠሩን ማህበረሰብ የሚያነቃቃና የግብርና ስራዎቹን እንደሚያሳድግም ተናግረዋል።
ዜጎች ይመክራሉ ኢትዮጵያ ትድናለች-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Jul 26, 2026 91
ሀገር በብርቱ ዜጎቿ ጥረት የምትገነባ የጋራ ቤት ናት።የጋራ ቤታችን ኢትዮጵያን በጸና አለት ላይ መገንባት ለቀጣዩ ትውልድ የተረጋጋ ማኅበራዊ ቁርኝትን ይፈጥራል።ምክክርን ባሕል ማድረግ ደግሞ ሰላምን አንግሦ ሀገራዊ መግባባትን ያጠናክራል። ኢትዮጵያዊያን የጋራ ቤታቸውን ሊያጸኑ፣ ማኅበራዊ ውላቸውንም ሊያንጹ የሀሳብ የበላይነትን ማዕከል አድርገው እየተመካከሩ ነው። በምክክር ጉባኤው በርካታ አመለካከቶች በምክንያት እየቀረቡ ነው።ተቃራኒ ሀሳቦች በአመክንዮ እየተስተናገዱ ነው። አንዱ የሌላውን ብሶት እያዳመጠ ቀስ በቀስ የመግባባት ጎዳና እየተጠረገ ነው። በእርግጥም ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሰላማዊ መንገድ መነጋገር እንደሚችሉ በተግባር እየታየ ነው። ኢትዮጵያ መሸከም የማትችለው ግጭትና አለመግባባትን እንጂ መመካከርን እንዳልኾነ ልጆቿ እያስመሰከሩ ነው። የኢትዮጵያ ልጆች እናት ሀገራቸውን በሀሳብ ተዋፅኦ ሊያጸኑ ብዕር፣ ወረቀትና አዕምሯቸውን አሰናድተው በመመካከር ላይ ናቸው። ያለመግባባት መንስኤዎች ተለይተው የመፍትሔ ሀሳቦች ሲቀርቡ ሀገራችንን ያሳመሙ ሰንኮፎች አንድ በአንድ ይወገዳሉ። በምክክር ጉባኤው ላይ እየታየ ያለው እውነታም ይኸው ነው። ኢትዮጵያዊያን የመንግሥት አስተዳደርን፣ ማኅበራዊ ቁርኝትን፣ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታን፣ ፍትሕና ርትዕን የተመለከቱ ቁልፍ ሀገራዊ ጉዳዮችን አንስተው መወያየታቸው በዘላቂነት የሀገር ባለቤትነት ስሜታቸውን እንደሚያጠናክር ይጠበቃል። ተመካካሪዎች የሀሳብ ገደብ የለባቸውም። የልባቸውን አውጥተው ለመናገር ቋንቋም አያግዳቸውም።ኹሉም በሚችለው ቋንቋ ሀሳቡን እየገለጸ ነው። የሚነሱ ሀሳቦች በርካታ ቢኾኑም ማዕከላቸው ሀገር ነው። ኢትዮጵያችን በልጆቿ ምክክር ሕመሞቿን የምታድንበት ጉባኤ አካታችነትን፣ መደማመጥን እና አመክንዮን አንግቦ እየተጓዘ ነው። ዜጎች የሀገር ባለቤትነታቸው በተግባር የሚረጋገጠው በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነው። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያዊያን በጋራ አስተሳስረው የሚያኖሯቸውን ሕጎች፣ አሠራሮች፣ አደረጃጀቶች፣ የሀሳብ መሠረቶች የሚያድሱበት ብሎም የሚነድፉበት በመኾኑ ኢትዮጵያን ያክማታል። ኢትዮጵያን ያሳመማት አለመግባባት፣ የሚያክሟት ደግሞ ዜጎቿ ናቸው። በዜጎች ልባዊ ምክክር ኢትዮጵያ ከሕመሟ ትድናለች!
ፖለቲካ
በአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ የሚሳተፉ ልዑካን አዲስ አበባ መግባት ጀመሩ
Jul 26, 2026 65
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦በ49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ለመሳተፍ የአፍሪካ ሀገራት ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በዚሁ መሠረት የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ዶክተር ኤድዋርድ ቢዚማና አዲስ አበባ ገብተዋል። አምባሳደር ዶክተር ኤድዋርድ ቢዚማና ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ሹም መላኩ በዳዳ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። 49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ከሐምሌ 21 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል። በጉባኤው ለመሳተፍ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች እና የልዑካን ቡድን አባላትም አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ።
ዜጎች ይመክራሉ ኢትዮጵያ ትድናለች-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Jul 26, 2026 91
ሀገር በብርቱ ዜጎቿ ጥረት የምትገነባ የጋራ ቤት ናት።የጋራ ቤታችን ኢትዮጵያን በጸና አለት ላይ መገንባት ለቀጣዩ ትውልድ የተረጋጋ ማኅበራዊ ቁርኝትን ይፈጥራል።ምክክርን ባሕል ማድረግ ደግሞ ሰላምን አንግሦ ሀገራዊ መግባባትን ያጠናክራል። ኢትዮጵያዊያን የጋራ ቤታቸውን ሊያጸኑ፣ ማኅበራዊ ውላቸውንም ሊያንጹ የሀሳብ የበላይነትን ማዕከል አድርገው እየተመካከሩ ነው። በምክክር ጉባኤው በርካታ አመለካከቶች በምክንያት እየቀረቡ ነው።ተቃራኒ ሀሳቦች በአመክንዮ እየተስተናገዱ ነው። አንዱ የሌላውን ብሶት እያዳመጠ ቀስ በቀስ የመግባባት ጎዳና እየተጠረገ ነው። በእርግጥም ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሰላማዊ መንገድ መነጋገር እንደሚችሉ በተግባር እየታየ ነው። ኢትዮጵያ መሸከም የማትችለው ግጭትና አለመግባባትን እንጂ መመካከርን እንዳልኾነ ልጆቿ እያስመሰከሩ ነው። የኢትዮጵያ ልጆች እናት ሀገራቸውን በሀሳብ ተዋፅኦ ሊያጸኑ ብዕር፣ ወረቀትና አዕምሯቸውን አሰናድተው በመመካከር ላይ ናቸው። ያለመግባባት መንስኤዎች ተለይተው የመፍትሔ ሀሳቦች ሲቀርቡ ሀገራችንን ያሳመሙ ሰንኮፎች አንድ በአንድ ይወገዳሉ። በምክክር ጉባኤው ላይ እየታየ ያለው እውነታም ይኸው ነው። ኢትዮጵያዊያን የመንግሥት አስተዳደርን፣ ማኅበራዊ ቁርኝትን፣ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታን፣ ፍትሕና ርትዕን የተመለከቱ ቁልፍ ሀገራዊ ጉዳዮችን አንስተው መወያየታቸው በዘላቂነት የሀገር ባለቤትነት ስሜታቸውን እንደሚያጠናክር ይጠበቃል። ተመካካሪዎች የሀሳብ ገደብ የለባቸውም። የልባቸውን አውጥተው ለመናገር ቋንቋም አያግዳቸውም።ኹሉም በሚችለው ቋንቋ ሀሳቡን እየገለጸ ነው። የሚነሱ ሀሳቦች በርካታ ቢኾኑም ማዕከላቸው ሀገር ነው። ኢትዮጵያችን በልጆቿ ምክክር ሕመሞቿን የምታድንበት ጉባኤ አካታችነትን፣ መደማመጥን እና አመክንዮን አንግቦ እየተጓዘ ነው። ዜጎች የሀገር ባለቤትነታቸው በተግባር የሚረጋገጠው በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነው። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያዊያን በጋራ አስተሳስረው የሚያኖሯቸውን ሕጎች፣ አሠራሮች፣ አደረጃጀቶች፣ የሀሳብ መሠረቶች የሚያድሱበት ብሎም የሚነድፉበት በመኾኑ ኢትዮጵያን ያክማታል። ኢትዮጵያን ያሳመማት አለመግባባት፣ የሚያክሟት ደግሞ ዜጎቿ ናቸው። በዜጎች ልባዊ ምክክር ኢትዮጵያ ከሕመሟ ትድናለች!
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የተሻለች ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ ለማስረከብ ትልቅ ምዕራፍ ነው
Jul 26, 2026 115
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የተሻለች ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ ለማስረከብ ትልቅ ምዕራፍ ነው ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት አጀንዳዎች በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዋናውን ምክክር እያካሄደ ይገኛል። የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር አቶ መስዑድ ገበየሁ እንደገለጹት፤ ለረጅም ጊዜ ስር የሰደዱ ችግሮችን ለመፍታት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው መካሄድ መጀመሩ ትልቅ እርምጃና ስኬት ነው። ኅብረቱ ከአስር በላይ ታዛቢዎችን በማሰማራት ባደረገው ትዝብት፤ በምክክር መድረኩ ላይ የብዙሃን ማኅበረሰብ ተወካዮች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በንቃት ሀሳብ ሲያንሸራሽሩ መታዘቡን አብራርተዋል። ኮሚሽኑ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ ዜጎች በቋንቋቸው ሀሳባቸውን በነጻነት እንዲገልጹና እንዲያዳምጡ አስተርጓሚዎችን ማዘጋጀቱ የሚበረታታ ተግባር መሆኑን አክለዋል። የተመካካሪዎች ንቁ ተሳትፎ በአጀንዳዎቹ ላይ የጋራ ፖለቲካዊ መግባባት በመፍጠር ረገድ ለተቋማዊ መፍትሔ መገኘት ከፍተኛ አጋዥ እንደሚሆን ገልጸዋል። ተመካካሪ ኡስማን መሐመድ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በየደረጃው የሚገኙ ዜጎችን ያሳተፈ በመሆኑ ከሌሎች ሀገራት የምክክር ተሞክሮ ልዩ ያደርገዋል። የምክክሩ ሂደቱ አካታችነት በተግባር ማረጋገጡን ጠቁመው፣ ስር በሰደዱ ችግሮች ዙሪያ መግባባት ላይ ለመድረስ የተጀመረው ሂደት ተስፋ ሰጪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አጀንዳዎቹም ከማህበረሰቡ የተሰበሰቡ በመሆናቸው፤ ከመድረኩ ሀገርን ወደ ተሻለ እድገት የሚያሸጋገር መፍትሔ ይገኛል የሚል ሙሉ እምነት እንዳላቸው አብራርተዋል። በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ቀደምት ትውልዶች ያላገኙት ትልቅ ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅሰው ትውልድን ወደፊት የሚያሸጋግር የጋራ ዓላማ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣዩ ትውልድ የምትመች እና የጸናች ኢትዮጵያን ለመገንባት መሰረት የሚጥል ነው
Jul 26, 2026 117
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ የመደማመጥና የጋራ መግባባት ባህልን በማጠናከር ለቀጣዩ ትውልድ የምትመች እና የጸናች ኢትዮጵያን ለመገንባት መሰረት የሚጥል መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መጀመሩ ይታወሳል። ያለልዩነት ሁሉንም አሳታፊ ያደረገው ይህ የምክክር መድረክ ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን በሰለጠነ መንገድ በመመካከር መፍተሄ ለማበጀት ትልቅ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኗል። በመሆኑም ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም እና ልማት የጸና መሰረት እንደሚጥልም ይጠበቃል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ተመካካሪዎች የምክክር ጉባዔው በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም እና ዕድገት ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ሰለሞን ታፈሰ እንዳሉት፣ ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ያሳተፈና ተመካክሮ ሀገርን በሰላም ማስቀጠል እንደሚቻል በግልጽ ያየንበት ታሪካዊ መድረክ ነው ብለዋል። መድረኩ አለመግባባቶች ላይ በግልጽ እና በነጻነት ለመመካከር ሰፊ ዕድል የፈጠረ በመሆኑ እውነተኛ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል። ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል ተመካካሪዎች የተገኙበት መድረክ በመሆኑም ይበልጥ ለመተዋወቅ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ተመካካሪ አቶ ነጻነት ጣሰው በበኩላቸው፥ ሀገራዊ ምክክሩ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሌሎችንም ባለድርሻዎች በሙሉ ያቀፈ በመሆኑ የሂደቱን አካታችነት በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ምክክሩ በበርካታ ጉዳዮች ላይ በሰከነ መንፈስ በመመካከር እና በመደማመጥ ሁሉም እኩል የሚሳተፍበትን መልካም አጋጣሚ መፍጠሩንም አንስተዋል። ይህ ታሪካዊ የምክክር ሂደት የመደማመጥና የጋራ መግባባት ባህልን በማጠናከር የተሻለች እና በዴሞክራሲ የጸናች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል መሆኑን አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የቆዩ ችግሮች የሚፈቱበት እና ዘላቂ መፍትሔ የሚያገኙበት ታሪካዊ መድረክ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ተመካካሪ አቶ አሰፋ ወዳጆ ናቸው። ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን በጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ ለመመካከርና ሕብረብሔራዊ አንድነታቸውን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ድንቅ አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል። በምክክሩ የሚደረስበት መግባባት ኢትዮጵያ ለምታልመው የሰላም ግንባታ መሰረት በመጣል፣ በአፍሪካ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የተምሳሌትነት ሚና ከፍ አድርጎ እንደሚያስቀጥል እምነታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የሚሰጠንን ማንኛውም ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ዝግጁ ነን
Jul 25, 2026 407
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የሚሰጣቸውን ማንኛውም ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተመራቂ መኮንኖች ገለጹ። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ያሰለጠናቸውን 71ኛ ዙር መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖች አስመርቋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጀነራል ይመር መኮንን፣ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ጌታቸው ሃብታሙ፣ ጄኔራል መኮንኖች እና የሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። በዚህ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመራቂ መኮንኖች በስልጠናው ያገኙትን ንድፈ ሃሳብ ከተግባር ያጣመረ ዕውቀትና ክህሎት በመጠቀም የሀገራቸውን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከተመራቂ መኮንኖቹ መካከል የዋንጫ ተሸላሚው ምክትል መቶ አለቃ ዳዊት አዱኛ አንደገለጹት፤ በሶስት ዓመታት ወታደራዊ ስልጠና ሀገራቸውን በብቃት ማገልገል የሚያስችል ዕውቀት ቀስመዋል። ከስልጠና ባገኙት እውቀትና ክህሎት መሰረትም ኢትዮጵያን ለማገልገል የሚሰጣቸውን ማንኛውም ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሌላው የሜዳሊያ ተሸላሚ ምክትል መቶ አለቃ ጌትነት አፈለ በበኩላቸው፤ በስልጠናው ኢትዮጵያን ሀገሬን በብቃት የማገለግልበትን ወታደራዊ ዕውቀት አግኝቻለሁ ብለዋል። በስልጠናው ያገኙትን የዕውቀት፣ የአስተሳሰብና ክህሎት ብቃት ለሀገራቸው መልሰው ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዕድገትና ብልፅግና ጎዳና ላይ በመሆኗ የሀገሪቱን ልማት ለማደናቀፍ የሚሹ የጥፋት ኃይሎችን ተልዕኮ ለማምከን ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። በቆይታቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ክብር ማስጠበቅ የሚያስችል ወታደራዊ ዕውቀት መቅሰማቸውን ያነሱት ደግሞ ምክትል መቶ አለቃ ኦብሳ ሰይፉ ናቸው። የሀገራቸውን ዳር ድንበር ለማስጠበቅ ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሀገረ መንግሥት ግንባታን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል ነው
Jul 25, 2026 357
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው አካታች ሀገራዊ የምክክር ሂደት የሀገረ መንግሥት ግንባታን ለማጠናከር፣ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና የሕዝቦችን አንድነት ማረጋገጥ የሚያስችል ታላቅ ዕድል መሆኑን ተመካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት አጀንዳዎች በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዋናውን ምክክር እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የተጀመረው ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያውያን በመመካከር ሀገራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን መሠረት የሚጥል ነው። በምክክር መድረኩ እየተመካከሩ የሚገኙና አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ፖለቲከኞች እንዳመለከቱት፤ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ለሰላምና ለፍትህ በርካታ ትግሎች የተደረጉ ቢሆንም የሚፈለገው ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት መገንባት አልተቻሉም። አሁን ላይ የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ግን ዜጎች በነፃነት የሚወያዩበትና በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን ነው የተናገሩት። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ጎበዜ አበራ እንደገለጹት፤ ይህ እጅግ አካታችና የመላዋን ኢትዮጵያ ስብጥርና ብዝሃነት ያከበረ መድረክ፣ በሀገራችን ባልተለመደ መልኩ ችግሮችን ተነጋግሮ የመፍታት አዲስ ባህልና ሥርዓት ለመገንባት ትልቅ ተስፋ ሰንቋል። በሂደቱ በዋና ዋና መዋቅራዊ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ መግባባት ይፈጠራል ብለን እንጠብቃለን ሲሉም ገልጸዋል። የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ዋና ፀሀፊ ሙሉብርሃን ኃይሉ፤ በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ አማካኝነት ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት እና ተቋማት እንደሚፈጠሩና በየደረጃው ያሉ መዋቅራዊ ችግሮች ደረጃ በደረጃ እንደሚፈቱ እምነታቸው መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ሀገሪቱ ወደ ሙሉ ሰላም፣ መረጋጋት እና ዘላቂ አንድነት እንደሚያሸጋግራት አክለዋል። የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ፕሬዚዳንት አላምረው ይርዳው እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር ቀደምት ትውልዶች ያላገኙትን ትልቅ ታሪካዊ አጋጣሚ ያመቻቸ ነው። መላው ሕዝብ ትውልድን ወደፊት በሚያሸጋግር የጋራ ዓላማ ላይ በትብብር ሊሠራ እንደሚገባም ነው ጨምረው የገለጹት።
ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሚያግዝ ስምሪት ተደርጓል - የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት
Jul 25, 2026 424
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ለመገንባት የሚያግዝ ስምሪት ማድረጉን ገለጸ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መግለጫ፤ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸሙን በተመለከተ ባካሄደው ግምገማዊ ውይይት ጠንካራና የተረጋጋ ሀገረ-መንግሥት ለመፍጠር በሚያግዝ መልኩ የተሳካ ስምሪት ማድረጉን ገልጿል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት መጀመሪያ ዓለም አቀፋዊ፣ ቀጣናዊ እና ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን በጥልቀት በመገንዘብና ስጋቶችን አስቀድሞ በመተንተን ወደ ተግባር መገባቱን የጠቆመው የአገልግሎቱ መግለጫ፤ በተለይ የሰባተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ደኅንነት ማዕከል በማድረግ የተዘጋጀውን የበጀት ዓመቱን ቁልፍ ግብ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በማሳካት የጸና ሀገረ-መንግሥት የመገንባት ሂደቱ ላይ ጉልህ ሚና መጫወት መቻሉን ጠቁሟል፡፡ ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅሞች መከበርና ማደግ እንዲሁም ለዜጎች ደኅንነት ስጋት በሆኑ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ መንገዶች በመሰብሰብ፣በማደራጀትና በመተንተን ለውሳኔ ሰጪ አካላትና ለኦፕሬሽናል ግዳጆች ማዋል መቻሉ በመግለጫው ተመላክቷል፡፡ በዚህም የሽብርና ታጣቂ ቡድኖችን የመረጃ፣ የሎጂስቲክስ እና የሽብር መረብ በመበጣጠስና ምርጫውን በሰላማዊ መንገድ በማካሄድ እንደ ሀገር ተደቅነው የነበሩ በርካታ ስጋቶችን ማክሸፍ መቻሉን አስታውቋል፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ያስገኛቸውን ጥቅሞች በሚጻረር መልኩ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችንና የኢኮኖሚ አሻጥሮችን በመከላከል የዜጎችን መሠረታዊ ጥያቄዎች ለመመለስ በተከናወኑ የመረጃ ስምሪቶችና ኦፕሬሽኖች በርካታ በሕገ-ወጥ ተግባር የተሰማሩ ሰዎች ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው መደረጉንም መግለጫው ጠቅሷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በውጭ መረጃ ስምሪቱ የሀገሪቷን ብሔራዊ ጥቅሞች በላቀ ደረጃ የሚያረጋግጡ ስኬቶችን ማስመዝገቡን መግለጫው አብራርቷል፡፡ በዚህ ረገድ በቀጣናው እና በዓለም-አቀፍ ደረጃ የሚስተዋሉ የኃይል አሰላለፍ ለውጦችንና ጂኦ-ፖለቲካዊ አዝማሚያዎችን በመረዳትና በመተንተን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደኅንነት፣ ጥቅምና ክብር የሚያረጋግጡ አቅጣጫዎች ለመከተል የሚያግዙ ስትራቴጂካል መረጃዎች መሰብሰብና ማሰራጨት መቻሉና ተጨባጭ ለውጥ መገኘቱንም አስታውቋል፡፡ ከውጭ አቻ ተቋማት ጋር መርህን በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ የአጋርነትና ትብብር ሥራዎችም ሽብርተኝነትን፤ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችንና ሕገ-ወጥ የገንዘብና የጦር-መሣሪያ ዝውውሮችን በመከላከል ከፍተኛ ሚና እንዳበረከቱ አመልክቷል፡፡ አገልግሎቱ በበጀት ዓመቱ በደኅንነት ስምሪት ማዕቀፉ፣ ቁልፍ የመንግሥት ተቋማትን፣ እንደ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ስልታዊ መሰረተ-ልማቶችን እና ታላላቅ ሀገራዊ ኹነቶችን ደኅንነት በአስተማማኝ ሁኔታ የመጠበቅ አቅም እንደገነባ በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡ አስተማማኝ በሆነ መንገድ በቴክኖሎጂ ጭምር ታግዞ የተገነባው ደኅንነትን የማረጋገጥ ስርዓት ኢትዮጵያ ተመራጭ የኮንፈረስ ቱሪዝም ማዕከል እንድትሆን እገዛ ማድረጉም መግለጫው ገልጿል። የአቪዬሽን ደኅንነትን በማረጋገጥ ረገድ የተከናወኑ ሥራዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስተማማኝና ተመራጭ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽዖ እያደረገ መቀጠሉ በዓመታዊ ግምገማው ተነስቷል፡፡ ይህን ስኬት በአሠራርና በቴክኖሎጂ ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራትም ስኬታማ እንደነበሩ ተመላክቷል፡፡ የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅትና የሌሎችም ምዘና ተቋማትን ኦዲቶችን ያለምንም ጉድለት ማጠናቀቅ መቻሉና የአቪዬሽን ደኅንነት አዋጅ ተሻሽሎ መጽደቁም በአብነት የሚጠቀሱ ስኬቶች መሆናቸው በመግለጫው ተብራርቷል። እንደ ሀገር የሚቃጡ የሥነ-ልቦና ጦርነቶችን ለመመከትና ለማጥቃት በተሰጡት የማስተባበር ሥራዎች ከጠላት ኃይሎች የሚቃጡ ሙከራዎችን ከማክሸፍ ባሻገር፤ ሀገራዊ አንድነትንና ሕብረትን የሚያፀኑ እንዲሁም የኢትዮጵያን ገፅታ የሚገነቡ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውም በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለመረጃ፣ ለደኅንነትና ለሥነ-ልቦና ጦርነት ስምሪት የሚውሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በራስ አቅም በማበልፀግ የውጭ ጥገኝነትን ለመቀነስ የተከናወኑ ሥራዎች ከፍተኛ ተስፋ የሚሰጡ መሆናቸው መገምገሙ ተመላክቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መግለጫ እንዳመለከተው፤ በቀጣይ የላቀ አፈጻጸም ያለው ተቋም ለመገንባት የሚከናወኑትን ሥራዎች ለማጠናከር ሪፎርሙን በአዳዲስ ዕይታዎች የሚያበለፅጉ አቅጣጫዎች ተቀምጧል፡፡
መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያን ዕድገት የማይፈልጉ የጥፋት ኃይሎችን ተልዕኮ በማምከን ግዳጁን በአስተማማኝ ብቃት እየተወጣ ነው
Jul 25, 2026 531
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያን ዕድገት የማይፈልጉ የጥፋት ኃይሎችን ተልዕኮ በማምከን ግዳጁን በአስተማማኝ ብቃት እየተወጣ እንደሚገኝ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ያሰለጠናቸውን 71ኛ ዙር መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖች እያስመረቀ ይገኛል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጄኔራል ይመር መኮንን፣ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ጌታቸው ሃብታሙ፣ ጄኔራል መኮንኖችና የሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ባላት የጂኦ ፖለቲካ አቀማመጥና በተፈጥሮ ሃብቷ ምክንያት ለተለያዩ ፈተናዎች ስትጋለጥ የቆየች ሀገር ናት። አርበኞች በታሪክ የሀገራቸውን ህልውና በመጠበቅ የተጫወቱትን ሚና በማስታወስ፤ በአሁኑ ወቅት የሀገርን ሰላምና ደኅንነት ለመፈታተን የሚሞክሩ ኃይሎች መኖራቸውን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በልማትና በብልፅግና ጉዞ ላይ መሆኗን የማይወዱ የጥፋት ኃይሎች ሴራና ደባ ለመፈጸም እየሞከሩ መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሀገር ፍቅር፣ በአርበኝነትና ሕዝብን የማገልገል ዕሴቶች በመላበስ ኢትዮጵያን ለማዳከም የሚቃጡ የጥፋት ሴራዎችን በብቃት እያመከነ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የሚገጥማትን ፈተና በድል ለመወጣት ከትውልድ ትውልድ የተላለፈ የወል ብቃት ያላት ሀገር መሆኗን በመጥቀስ። ይሁንና ዘመኑ የሚጠይቀውን የደኅንነት ፈተና ለመመከት የወል ብቃት ብቻ በቂ እንደማይሆን ጠቅሰው፤ ያለውን አቅም በሰው ኃይል ልማት፣ በትምህርትና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የመከላከያ ሠራዊት የማሰልጠንና የማብቃት ተልዕኮውን በማጠናከር በርካታ የስልጠና ተቋማትን በማስፋፋት የሰው ኃይል ልማት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም የሠራዊቱ የሙያ ብቃት፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የተልዕኮ አፈጻጸም አቅም እየጎለበተና እየዘመነ መምጣቱን ጠቁመዋል። የመከላከያ ትምህርትና ሥልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጄኔራል ይመር መኮንን በበኩላቸው፤ ዘመናዊ ሠራዊት ግንባታን እውን ማድረግ የሚያስችሉ የትምህርትና ስልጠና ማዕከላት ተገንብተዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚና ሌሎች የሥልጠና ማዕከላት ዘመኑን የዋጀ ሥርዓተ ትምህርት በመቅረፅ በቴክኖሎጂ፣ በአስተሳሰብ፣ በአሰራር የበቁ የሠራዊትና አመራር አባላት እየተፈጠሩ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በዛሬው ዕለት ያስመረቃቸው የ71ኛ መተማ ካዴት ዕጩ መኮንኖችም የዚህ ጥረት መገለጫዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ጌታቸው ሀብታሙ፤ ተመራቂዎቹ የወሰዱት ስልጠና ሁለንተናዊ የአመራር ጥንካሬን የሚያጎለብት መሆኑን ገልጸዋል። ዕጩ መኮንኖቹ ያገኙት ትምህርትና ስልጠና ማንኛውንም የሠራዊት የግዳጅ ተልዕኮ መወጣት የሚያስችል አቅም አጎናፅፏቸዋል ብለዋል። ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት በተጨማሪ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ አፍሪካውያን ዕጩ መኮንኖችም ስልጠናቸውን አጠናቀው መመረቃቸውን ተናግረዋል።
ፖለቲካ
በአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ የሚሳተፉ ልዑካን አዲስ አበባ መግባት ጀመሩ
Jul 26, 2026 65
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦በ49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ለመሳተፍ የአፍሪካ ሀገራት ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በዚሁ መሠረት የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ዶክተር ኤድዋርድ ቢዚማና አዲስ አበባ ገብተዋል። አምባሳደር ዶክተር ኤድዋርድ ቢዚማና ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ሹም መላኩ በዳዳ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። 49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ከሐምሌ 21 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል። በጉባኤው ለመሳተፍ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች እና የልዑካን ቡድን አባላትም አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ።
ዜጎች ይመክራሉ ኢትዮጵያ ትድናለች-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Jul 26, 2026 91
ሀገር በብርቱ ዜጎቿ ጥረት የምትገነባ የጋራ ቤት ናት።የጋራ ቤታችን ኢትዮጵያን በጸና አለት ላይ መገንባት ለቀጣዩ ትውልድ የተረጋጋ ማኅበራዊ ቁርኝትን ይፈጥራል።ምክክርን ባሕል ማድረግ ደግሞ ሰላምን አንግሦ ሀገራዊ መግባባትን ያጠናክራል። ኢትዮጵያዊያን የጋራ ቤታቸውን ሊያጸኑ፣ ማኅበራዊ ውላቸውንም ሊያንጹ የሀሳብ የበላይነትን ማዕከል አድርገው እየተመካከሩ ነው። በምክክር ጉባኤው በርካታ አመለካከቶች በምክንያት እየቀረቡ ነው።ተቃራኒ ሀሳቦች በአመክንዮ እየተስተናገዱ ነው። አንዱ የሌላውን ብሶት እያዳመጠ ቀስ በቀስ የመግባባት ጎዳና እየተጠረገ ነው። በእርግጥም ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሰላማዊ መንገድ መነጋገር እንደሚችሉ በተግባር እየታየ ነው። ኢትዮጵያ መሸከም የማትችለው ግጭትና አለመግባባትን እንጂ መመካከርን እንዳልኾነ ልጆቿ እያስመሰከሩ ነው። የኢትዮጵያ ልጆች እናት ሀገራቸውን በሀሳብ ተዋፅኦ ሊያጸኑ ብዕር፣ ወረቀትና አዕምሯቸውን አሰናድተው በመመካከር ላይ ናቸው። ያለመግባባት መንስኤዎች ተለይተው የመፍትሔ ሀሳቦች ሲቀርቡ ሀገራችንን ያሳመሙ ሰንኮፎች አንድ በአንድ ይወገዳሉ። በምክክር ጉባኤው ላይ እየታየ ያለው እውነታም ይኸው ነው። ኢትዮጵያዊያን የመንግሥት አስተዳደርን፣ ማኅበራዊ ቁርኝትን፣ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታን፣ ፍትሕና ርትዕን የተመለከቱ ቁልፍ ሀገራዊ ጉዳዮችን አንስተው መወያየታቸው በዘላቂነት የሀገር ባለቤትነት ስሜታቸውን እንደሚያጠናክር ይጠበቃል። ተመካካሪዎች የሀሳብ ገደብ የለባቸውም። የልባቸውን አውጥተው ለመናገር ቋንቋም አያግዳቸውም።ኹሉም በሚችለው ቋንቋ ሀሳቡን እየገለጸ ነው። የሚነሱ ሀሳቦች በርካታ ቢኾኑም ማዕከላቸው ሀገር ነው። ኢትዮጵያችን በልጆቿ ምክክር ሕመሞቿን የምታድንበት ጉባኤ አካታችነትን፣ መደማመጥን እና አመክንዮን አንግቦ እየተጓዘ ነው። ዜጎች የሀገር ባለቤትነታቸው በተግባር የሚረጋገጠው በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነው። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያዊያን በጋራ አስተሳስረው የሚያኖሯቸውን ሕጎች፣ አሠራሮች፣ አደረጃጀቶች፣ የሀሳብ መሠረቶች የሚያድሱበት ብሎም የሚነድፉበት በመኾኑ ኢትዮጵያን ያክማታል። ኢትዮጵያን ያሳመማት አለመግባባት፣ የሚያክሟት ደግሞ ዜጎቿ ናቸው። በዜጎች ልባዊ ምክክር ኢትዮጵያ ከሕመሟ ትድናለች!
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የተሻለች ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ ለማስረከብ ትልቅ ምዕራፍ ነው
Jul 26, 2026 115
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የተሻለች ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ ለማስረከብ ትልቅ ምዕራፍ ነው ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት አጀንዳዎች በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዋናውን ምክክር እያካሄደ ይገኛል። የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር አቶ መስዑድ ገበየሁ እንደገለጹት፤ ለረጅም ጊዜ ስር የሰደዱ ችግሮችን ለመፍታት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው መካሄድ መጀመሩ ትልቅ እርምጃና ስኬት ነው። ኅብረቱ ከአስር በላይ ታዛቢዎችን በማሰማራት ባደረገው ትዝብት፤ በምክክር መድረኩ ላይ የብዙሃን ማኅበረሰብ ተወካዮች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በንቃት ሀሳብ ሲያንሸራሽሩ መታዘቡን አብራርተዋል። ኮሚሽኑ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ ዜጎች በቋንቋቸው ሀሳባቸውን በነጻነት እንዲገልጹና እንዲያዳምጡ አስተርጓሚዎችን ማዘጋጀቱ የሚበረታታ ተግባር መሆኑን አክለዋል። የተመካካሪዎች ንቁ ተሳትፎ በአጀንዳዎቹ ላይ የጋራ ፖለቲካዊ መግባባት በመፍጠር ረገድ ለተቋማዊ መፍትሔ መገኘት ከፍተኛ አጋዥ እንደሚሆን ገልጸዋል። ተመካካሪ ኡስማን መሐመድ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በየደረጃው የሚገኙ ዜጎችን ያሳተፈ በመሆኑ ከሌሎች ሀገራት የምክክር ተሞክሮ ልዩ ያደርገዋል። የምክክሩ ሂደቱ አካታችነት በተግባር ማረጋገጡን ጠቁመው፣ ስር በሰደዱ ችግሮች ዙሪያ መግባባት ላይ ለመድረስ የተጀመረው ሂደት ተስፋ ሰጪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አጀንዳዎቹም ከማህበረሰቡ የተሰበሰቡ በመሆናቸው፤ ከመድረኩ ሀገርን ወደ ተሻለ እድገት የሚያሸጋገር መፍትሔ ይገኛል የሚል ሙሉ እምነት እንዳላቸው አብራርተዋል። በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ቀደምት ትውልዶች ያላገኙት ትልቅ ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅሰው ትውልድን ወደፊት የሚያሸጋግር የጋራ ዓላማ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣዩ ትውልድ የምትመች እና የጸናች ኢትዮጵያን ለመገንባት መሰረት የሚጥል ነው
Jul 26, 2026 117
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ የመደማመጥና የጋራ መግባባት ባህልን በማጠናከር ለቀጣዩ ትውልድ የምትመች እና የጸናች ኢትዮጵያን ለመገንባት መሰረት የሚጥል መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መጀመሩ ይታወሳል። ያለልዩነት ሁሉንም አሳታፊ ያደረገው ይህ የምክክር መድረክ ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን በሰለጠነ መንገድ በመመካከር መፍተሄ ለማበጀት ትልቅ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኗል። በመሆኑም ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም እና ልማት የጸና መሰረት እንደሚጥልም ይጠበቃል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ተመካካሪዎች የምክክር ጉባዔው በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም እና ዕድገት ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ሰለሞን ታፈሰ እንዳሉት፣ ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ያሳተፈና ተመካክሮ ሀገርን በሰላም ማስቀጠል እንደሚቻል በግልጽ ያየንበት ታሪካዊ መድረክ ነው ብለዋል። መድረኩ አለመግባባቶች ላይ በግልጽ እና በነጻነት ለመመካከር ሰፊ ዕድል የፈጠረ በመሆኑ እውነተኛ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል። ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል ተመካካሪዎች የተገኙበት መድረክ በመሆኑም ይበልጥ ለመተዋወቅ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ተመካካሪ አቶ ነጻነት ጣሰው በበኩላቸው፥ ሀገራዊ ምክክሩ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሌሎችንም ባለድርሻዎች በሙሉ ያቀፈ በመሆኑ የሂደቱን አካታችነት በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ምክክሩ በበርካታ ጉዳዮች ላይ በሰከነ መንፈስ በመመካከር እና በመደማመጥ ሁሉም እኩል የሚሳተፍበትን መልካም አጋጣሚ መፍጠሩንም አንስተዋል። ይህ ታሪካዊ የምክክር ሂደት የመደማመጥና የጋራ መግባባት ባህልን በማጠናከር የተሻለች እና በዴሞክራሲ የጸናች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል መሆኑን አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የቆዩ ችግሮች የሚፈቱበት እና ዘላቂ መፍትሔ የሚያገኙበት ታሪካዊ መድረክ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ተመካካሪ አቶ አሰፋ ወዳጆ ናቸው። ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን በጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ ለመመካከርና ሕብረብሔራዊ አንድነታቸውን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ድንቅ አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል። በምክክሩ የሚደረስበት መግባባት ኢትዮጵያ ለምታልመው የሰላም ግንባታ መሰረት በመጣል፣ በአፍሪካ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የተምሳሌትነት ሚና ከፍ አድርጎ እንደሚያስቀጥል እምነታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የሚሰጠንን ማንኛውም ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ዝግጁ ነን
Jul 25, 2026 407
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የሚሰጣቸውን ማንኛውም ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተመራቂ መኮንኖች ገለጹ። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ያሰለጠናቸውን 71ኛ ዙር መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖች አስመርቋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጀነራል ይመር መኮንን፣ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ጌታቸው ሃብታሙ፣ ጄኔራል መኮንኖች እና የሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። በዚህ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመራቂ መኮንኖች በስልጠናው ያገኙትን ንድፈ ሃሳብ ከተግባር ያጣመረ ዕውቀትና ክህሎት በመጠቀም የሀገራቸውን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከተመራቂ መኮንኖቹ መካከል የዋንጫ ተሸላሚው ምክትል መቶ አለቃ ዳዊት አዱኛ አንደገለጹት፤ በሶስት ዓመታት ወታደራዊ ስልጠና ሀገራቸውን በብቃት ማገልገል የሚያስችል ዕውቀት ቀስመዋል። ከስልጠና ባገኙት እውቀትና ክህሎት መሰረትም ኢትዮጵያን ለማገልገል የሚሰጣቸውን ማንኛውም ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሌላው የሜዳሊያ ተሸላሚ ምክትል መቶ አለቃ ጌትነት አፈለ በበኩላቸው፤ በስልጠናው ኢትዮጵያን ሀገሬን በብቃት የማገለግልበትን ወታደራዊ ዕውቀት አግኝቻለሁ ብለዋል። በስልጠናው ያገኙትን የዕውቀት፣ የአስተሳሰብና ክህሎት ብቃት ለሀገራቸው መልሰው ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዕድገትና ብልፅግና ጎዳና ላይ በመሆኗ የሀገሪቱን ልማት ለማደናቀፍ የሚሹ የጥፋት ኃይሎችን ተልዕኮ ለማምከን ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። በቆይታቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ክብር ማስጠበቅ የሚያስችል ወታደራዊ ዕውቀት መቅሰማቸውን ያነሱት ደግሞ ምክትል መቶ አለቃ ኦብሳ ሰይፉ ናቸው። የሀገራቸውን ዳር ድንበር ለማስጠበቅ ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሀገረ መንግሥት ግንባታን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል ነው
Jul 25, 2026 357
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው አካታች ሀገራዊ የምክክር ሂደት የሀገረ መንግሥት ግንባታን ለማጠናከር፣ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና የሕዝቦችን አንድነት ማረጋገጥ የሚያስችል ታላቅ ዕድል መሆኑን ተመካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት አጀንዳዎች በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዋናውን ምክክር እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የተጀመረው ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያውያን በመመካከር ሀገራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን መሠረት የሚጥል ነው። በምክክር መድረኩ እየተመካከሩ የሚገኙና አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ፖለቲከኞች እንዳመለከቱት፤ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ለሰላምና ለፍትህ በርካታ ትግሎች የተደረጉ ቢሆንም የሚፈለገው ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት መገንባት አልተቻሉም። አሁን ላይ የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ግን ዜጎች በነፃነት የሚወያዩበትና በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን ነው የተናገሩት። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ጎበዜ አበራ እንደገለጹት፤ ይህ እጅግ አካታችና የመላዋን ኢትዮጵያ ስብጥርና ብዝሃነት ያከበረ መድረክ፣ በሀገራችን ባልተለመደ መልኩ ችግሮችን ተነጋግሮ የመፍታት አዲስ ባህልና ሥርዓት ለመገንባት ትልቅ ተስፋ ሰንቋል። በሂደቱ በዋና ዋና መዋቅራዊ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ መግባባት ይፈጠራል ብለን እንጠብቃለን ሲሉም ገልጸዋል። የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ዋና ፀሀፊ ሙሉብርሃን ኃይሉ፤ በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ አማካኝነት ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት እና ተቋማት እንደሚፈጠሩና በየደረጃው ያሉ መዋቅራዊ ችግሮች ደረጃ በደረጃ እንደሚፈቱ እምነታቸው መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ሀገሪቱ ወደ ሙሉ ሰላም፣ መረጋጋት እና ዘላቂ አንድነት እንደሚያሸጋግራት አክለዋል። የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ፕሬዚዳንት አላምረው ይርዳው እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር ቀደምት ትውልዶች ያላገኙትን ትልቅ ታሪካዊ አጋጣሚ ያመቻቸ ነው። መላው ሕዝብ ትውልድን ወደፊት በሚያሸጋግር የጋራ ዓላማ ላይ በትብብር ሊሠራ እንደሚገባም ነው ጨምረው የገለጹት።
ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሚያግዝ ስምሪት ተደርጓል - የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት
Jul 25, 2026 424
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ለመገንባት የሚያግዝ ስምሪት ማድረጉን ገለጸ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መግለጫ፤ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸሙን በተመለከተ ባካሄደው ግምገማዊ ውይይት ጠንካራና የተረጋጋ ሀገረ-መንግሥት ለመፍጠር በሚያግዝ መልኩ የተሳካ ስምሪት ማድረጉን ገልጿል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት መጀመሪያ ዓለም አቀፋዊ፣ ቀጣናዊ እና ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን በጥልቀት በመገንዘብና ስጋቶችን አስቀድሞ በመተንተን ወደ ተግባር መገባቱን የጠቆመው የአገልግሎቱ መግለጫ፤ በተለይ የሰባተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ደኅንነት ማዕከል በማድረግ የተዘጋጀውን የበጀት ዓመቱን ቁልፍ ግብ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በማሳካት የጸና ሀገረ-መንግሥት የመገንባት ሂደቱ ላይ ጉልህ ሚና መጫወት መቻሉን ጠቁሟል፡፡ ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅሞች መከበርና ማደግ እንዲሁም ለዜጎች ደኅንነት ስጋት በሆኑ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ መንገዶች በመሰብሰብ፣በማደራጀትና በመተንተን ለውሳኔ ሰጪ አካላትና ለኦፕሬሽናል ግዳጆች ማዋል መቻሉ በመግለጫው ተመላክቷል፡፡ በዚህም የሽብርና ታጣቂ ቡድኖችን የመረጃ፣ የሎጂስቲክስ እና የሽብር መረብ በመበጣጠስና ምርጫውን በሰላማዊ መንገድ በማካሄድ እንደ ሀገር ተደቅነው የነበሩ በርካታ ስጋቶችን ማክሸፍ መቻሉን አስታውቋል፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ያስገኛቸውን ጥቅሞች በሚጻረር መልኩ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችንና የኢኮኖሚ አሻጥሮችን በመከላከል የዜጎችን መሠረታዊ ጥያቄዎች ለመመለስ በተከናወኑ የመረጃ ስምሪቶችና ኦፕሬሽኖች በርካታ በሕገ-ወጥ ተግባር የተሰማሩ ሰዎች ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው መደረጉንም መግለጫው ጠቅሷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በውጭ መረጃ ስምሪቱ የሀገሪቷን ብሔራዊ ጥቅሞች በላቀ ደረጃ የሚያረጋግጡ ስኬቶችን ማስመዝገቡን መግለጫው አብራርቷል፡፡ በዚህ ረገድ በቀጣናው እና በዓለም-አቀፍ ደረጃ የሚስተዋሉ የኃይል አሰላለፍ ለውጦችንና ጂኦ-ፖለቲካዊ አዝማሚያዎችን በመረዳትና በመተንተን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደኅንነት፣ ጥቅምና ክብር የሚያረጋግጡ አቅጣጫዎች ለመከተል የሚያግዙ ስትራቴጂካል መረጃዎች መሰብሰብና ማሰራጨት መቻሉና ተጨባጭ ለውጥ መገኘቱንም አስታውቋል፡፡ ከውጭ አቻ ተቋማት ጋር መርህን በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ የአጋርነትና ትብብር ሥራዎችም ሽብርተኝነትን፤ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችንና ሕገ-ወጥ የገንዘብና የጦር-መሣሪያ ዝውውሮችን በመከላከል ከፍተኛ ሚና እንዳበረከቱ አመልክቷል፡፡ አገልግሎቱ በበጀት ዓመቱ በደኅንነት ስምሪት ማዕቀፉ፣ ቁልፍ የመንግሥት ተቋማትን፣ እንደ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ስልታዊ መሰረተ-ልማቶችን እና ታላላቅ ሀገራዊ ኹነቶችን ደኅንነት በአስተማማኝ ሁኔታ የመጠበቅ አቅም እንደገነባ በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡ አስተማማኝ በሆነ መንገድ በቴክኖሎጂ ጭምር ታግዞ የተገነባው ደኅንነትን የማረጋገጥ ስርዓት ኢትዮጵያ ተመራጭ የኮንፈረስ ቱሪዝም ማዕከል እንድትሆን እገዛ ማድረጉም መግለጫው ገልጿል። የአቪዬሽን ደኅንነትን በማረጋገጥ ረገድ የተከናወኑ ሥራዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስተማማኝና ተመራጭ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽዖ እያደረገ መቀጠሉ በዓመታዊ ግምገማው ተነስቷል፡፡ ይህን ስኬት በአሠራርና በቴክኖሎጂ ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራትም ስኬታማ እንደነበሩ ተመላክቷል፡፡ የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅትና የሌሎችም ምዘና ተቋማትን ኦዲቶችን ያለምንም ጉድለት ማጠናቀቅ መቻሉና የአቪዬሽን ደኅንነት አዋጅ ተሻሽሎ መጽደቁም በአብነት የሚጠቀሱ ስኬቶች መሆናቸው በመግለጫው ተብራርቷል። እንደ ሀገር የሚቃጡ የሥነ-ልቦና ጦርነቶችን ለመመከትና ለማጥቃት በተሰጡት የማስተባበር ሥራዎች ከጠላት ኃይሎች የሚቃጡ ሙከራዎችን ከማክሸፍ ባሻገር፤ ሀገራዊ አንድነትንና ሕብረትን የሚያፀኑ እንዲሁም የኢትዮጵያን ገፅታ የሚገነቡ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውም በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለመረጃ፣ ለደኅንነትና ለሥነ-ልቦና ጦርነት ስምሪት የሚውሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በራስ አቅም በማበልፀግ የውጭ ጥገኝነትን ለመቀነስ የተከናወኑ ሥራዎች ከፍተኛ ተስፋ የሚሰጡ መሆናቸው መገምገሙ ተመላክቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መግለጫ እንዳመለከተው፤ በቀጣይ የላቀ አፈጻጸም ያለው ተቋም ለመገንባት የሚከናወኑትን ሥራዎች ለማጠናከር ሪፎርሙን በአዳዲስ ዕይታዎች የሚያበለፅጉ አቅጣጫዎች ተቀምጧል፡፡
መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያን ዕድገት የማይፈልጉ የጥፋት ኃይሎችን ተልዕኮ በማምከን ግዳጁን በአስተማማኝ ብቃት እየተወጣ ነው
Jul 25, 2026 531
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያን ዕድገት የማይፈልጉ የጥፋት ኃይሎችን ተልዕኮ በማምከን ግዳጁን በአስተማማኝ ብቃት እየተወጣ እንደሚገኝ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ያሰለጠናቸውን 71ኛ ዙር መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖች እያስመረቀ ይገኛል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጄኔራል ይመር መኮንን፣ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ጌታቸው ሃብታሙ፣ ጄኔራል መኮንኖችና የሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ባላት የጂኦ ፖለቲካ አቀማመጥና በተፈጥሮ ሃብቷ ምክንያት ለተለያዩ ፈተናዎች ስትጋለጥ የቆየች ሀገር ናት። አርበኞች በታሪክ የሀገራቸውን ህልውና በመጠበቅ የተጫወቱትን ሚና በማስታወስ፤ በአሁኑ ወቅት የሀገርን ሰላምና ደኅንነት ለመፈታተን የሚሞክሩ ኃይሎች መኖራቸውን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በልማትና በብልፅግና ጉዞ ላይ መሆኗን የማይወዱ የጥፋት ኃይሎች ሴራና ደባ ለመፈጸም እየሞከሩ መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሀገር ፍቅር፣ በአርበኝነትና ሕዝብን የማገልገል ዕሴቶች በመላበስ ኢትዮጵያን ለማዳከም የሚቃጡ የጥፋት ሴራዎችን በብቃት እያመከነ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የሚገጥማትን ፈተና በድል ለመወጣት ከትውልድ ትውልድ የተላለፈ የወል ብቃት ያላት ሀገር መሆኗን በመጥቀስ። ይሁንና ዘመኑ የሚጠይቀውን የደኅንነት ፈተና ለመመከት የወል ብቃት ብቻ በቂ እንደማይሆን ጠቅሰው፤ ያለውን አቅም በሰው ኃይል ልማት፣ በትምህርትና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የመከላከያ ሠራዊት የማሰልጠንና የማብቃት ተልዕኮውን በማጠናከር በርካታ የስልጠና ተቋማትን በማስፋፋት የሰው ኃይል ልማት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም የሠራዊቱ የሙያ ብቃት፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የተልዕኮ አፈጻጸም አቅም እየጎለበተና እየዘመነ መምጣቱን ጠቁመዋል። የመከላከያ ትምህርትና ሥልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጄኔራል ይመር መኮንን በበኩላቸው፤ ዘመናዊ ሠራዊት ግንባታን እውን ማድረግ የሚያስችሉ የትምህርትና ስልጠና ማዕከላት ተገንብተዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚና ሌሎች የሥልጠና ማዕከላት ዘመኑን የዋጀ ሥርዓተ ትምህርት በመቅረፅ በቴክኖሎጂ፣ በአስተሳሰብ፣ በአሰራር የበቁ የሠራዊትና አመራር አባላት እየተፈጠሩ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በዛሬው ዕለት ያስመረቃቸው የ71ኛ መተማ ካዴት ዕጩ መኮንኖችም የዚህ ጥረት መገለጫዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ጌታቸው ሀብታሙ፤ ተመራቂዎቹ የወሰዱት ስልጠና ሁለንተናዊ የአመራር ጥንካሬን የሚያጎለብት መሆኑን ገልጸዋል። ዕጩ መኮንኖቹ ያገኙት ትምህርትና ስልጠና ማንኛውንም የሠራዊት የግዳጅ ተልዕኮ መወጣት የሚያስችል አቅም አጎናፅፏቸዋል ብለዋል። ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት በተጨማሪ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ አፍሪካውያን ዕጩ መኮንኖችም ስልጠናቸውን አጠናቀው መመረቃቸውን ተናግረዋል።
ማህበራዊ
ኢትዮጵያ በአይነቱ ለየት ያለ የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን ሲምፖዚየም ታስተናግዳለች
Jul 26, 2026 60
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ከፍተኛ ትኩረት የሚስብ የ2026 የአፍሪካ ሎጂስቲክስና ኮሙኒኬሽን ሲምፖዚየም (African Logistics and Communication Symposium) ከሃምሌ 20 እስከ 25 ቀን በአዲስ አበባ ታስተናግዳለች። በሲምፖዚየሙ 40 ሀገራትና 26 ዋና ዋና አለም አቀፍ የኢንዱስትሪ አጋሮች ይሳተፉበታል ተብሎ ይጠበቃል። ዝግጅቱን በማስመልከት የመከላከያ የውጭ ግንኙነት እና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክትሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ እና በአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ (አፍሪኮም) የሎጂስቲክስ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀነራል ፓል ፍሪክና ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የመከላከያ የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ፤በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ሎጂስቲክስና ኮሙኒዩኬሽን ሲምፖዚየም ኢትዮጵያ ለዚህ ታላቅ አህጉራዊ መድረክ አስተናጋጅ ሆና መመረጧ በቀጠናው ለሰላም ያበረከተችው አስተዋፅኦ፣ በመንግሥት የተመዘገበው የልማት ውጤት፣ የአዲስ አበባ ከተማ እያሳየች ያለው ፈጣን እድገት እና ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን የማስተናገድ አቅሟ የፈጠረው ውጤት መሆኑንም ጠቁመዋል። ሲምፖዚየሙ በአሜሪካና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የትብብር ግንኙነት የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ በአፍሪካ የመከላከያ ተቋማት መካከል የልምድ ልውውጥና የጋራ ትብብር የሚያጎለብቱበት መድረክ መሆኑን አመልክተዋል። ሎጂስቲክስና ኮሙኒዩኬሽን በማንኛውም ወታደራዊም ሆነ ሰላማዊ ተልዕኮ ስኬት ውስጥ ወሳኝ ሚና ያላቸው ዘርፎች መሆናቸውን የገለፁት ዳይሬክተሩ ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ፣ የተሻሉ አሠራሮችን በመቅሰም እና ለወደፊት የሚያጋጥሙ የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን ችግሮች የጋራ መፍትሔ ለማፈላለግ ወሳኝ አጋጣሚ መሆኑን ጠቁመዋል። ከአጋር ሀገራት የሚገኙ ልምዶችና ዕውቀቶች ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅምን ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ገልጸው፣ እንደዚሁም ኢትዮጵያም ያላትን ልምድ ለአጋር ሀገራት በማካፈል በአህጉራዊ ሰላምና ደህንነት ዘርፍ ያላትን አስተዋፅኦ የበለጠ እንደምታጠናክር ገልጸዋል። የአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (AFRICOM) የሎጂስቲክስ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀነራል ፖል ፍሊክስ በበኩላቸው፥ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የ2026 የአፍሪካ ሎጂስቲክስና ኮሙኒዩኬሽን ሲምፖዚየምን በጋራ በማዘጋጀቷ ከፍተኛ ደስታና ክብር እንደሚሰማቸው ገልፀው፣ ለሲምፖዚየሙ መሳካት ኢትዮጵያ ያደረገችውን ዝግጅት አድንቀዋል። ኮንፍረንሱ በአሜሪካና በአፍሪካ መካከል በሎጂስቲክስና በኮሙኒዩኬሽን ዘርፍ ያለውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እንደሚሆንም ጠቁመዋል። በቀጣዮቹ ቀናት ተሳታፊ ሀገራት የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅሞቻቸውን በመገምገም፣ ያሉ ክፍተቶችንና ተግዳሮቶችን በጋራ በመለየት ዘላቂ መፍትሔዎችን ለማፍለቅ እንደሚሠሩም ገልጸዋል። ሲምፖዚየሙ በትብብር፣ በፈጠራና በጋራ ትምህርት የተሞላ ፍሬያማ ሳምንት እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልጸው፣ በጋራ በመሥራት ጠንካራ የትስስር መረቦችን በመገንባት የሀገራትን አቅም ከፍ ማድረግና ለበለጠ ደህንነትና ብልጽግና መሠረት መጣል እንደሚቻል ተናግረዋል። በመጨረሻም ኢትዮጵያ ለዚህ ዓይነት ታላቅ አህጉራዊ ጉባኤ አስተናጋጅ ሆና መመረጧ ለመከላከያና ለሀገሪቱ ትልቅ ክብር መሆኑን ገልጸው፣ ለዚህ ስኬት አስተዋፅኦ ላበረከቱ የመከላከያ አመራሮች፣ የመንግሥት ተቋማት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምስጋና ማቅረባቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
ሀገራዊ ምክክሩ የልጄም የነገ ተስፋ ጭምር የሚሰራበት ነው
Jul 26, 2026 82
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ የልጄም የነገ ተስፋ ጭምር የሚሰራበት በመሆኑ ጤናዬ በፈቀደው ልክ እስከመጨረሻው ተሳትፌ አላማዬን አሳካለሁ ሲሉ በምክክር ጉባዔው ላይ ልጅ የወለዱት ሁለተኛዋ እናት ሀዳ አልመሀዲ ገልጸዋል። እናት ሀዳ አልመሀዲ ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን ብሎም የልጆቻችንን የነገ ተስፋ ብሩህ የሚያደርግ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ምንም እንኳን ቀኔ የደረሰ ነብሰ ጡር ብሆንም ጉባኤው ላይ በመሳተፍ ሀላፊነቴን ልወጣ መጥቼ በዚህ ሂደት ላይ እያለሁ የልጅ እናት መሆን ችያለሁ ሲሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በተመረጡት አጀንዳዎች ላይ ተጠናክሮ እየተካሄደ ሲሆን በርካታ አስገራሚ ጉዳዮችም እየታዩበት ይገኛሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ አንዱ ደግሞ የእነ አቶ አብዱልወኪል ከማል እና ወይዘሮ ሀዳ አልመሀዲ ቤተሰብ ታሪክ ተጠቃሽ ነው፡፡ ባል አቶ አብዱልወኪል ከማል የብልጽግና ፓርቲ አባል ሲሆኑ ባለቤታቸው ወይዘሮ ሀዳ አልመሀዲ ደግሞ የተፎካካሪው የቤንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ ቤህነን ፓርቲ አመራር ናቸው፡፡ የግል የፖለቲካ አመለካከታቸውን በየግላቸው ይዘው የጋራ ትዳራቸውን የሚመሩት ጥንዶቹ ታዲያ ሚስት ወይዘሮ ሀዳ ፓርቲያቸውን ወክለው በምክክሩ እንዲሳተፉ በጋራ መግባባት ወስነዋል፡፡ ወይዘሮ ሀዳ አልመሀዲ በምክክሩ ሂደት ልጅ የወለዱ ሁለተኛዋ እናት ሲሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር ጋር በመሆን በኢትዮጵያዊ ባህል ወይዘሮ ሀዳን አራስ ጥሪ ይዘው መርቀዋቸዋል፡፡ ለወላዷ እናት ምክክሩ በሚካሄድበት አዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በሚገኘው ሆቴል ምቹ ማረፊያ እና አስፈላጊው እንክብካቤ እንዲደረግላቸውም ተደርጓል፡፡ እናት ሀዳም ታዲያ ከወሊድ ሂደቱ ጀምሮ እየተደረገልን ያለው እንክብካቤ ኢትዮጵያዊ መደጋግፍን በተግባር ያየንበት ነው ብለዋል፡፡ ምክክሩ የልጄም የነገ ተስፋ ጭምር የሚሰራበት በመሆኑ ጤናዬ በፈቀደው ልክ እስከመጨረሻው ተሳትፌ አላማዬን አሳካለሁ ሲሉም ገልጸዋል፡፡ አቶ አብዱልወኪል ከማል እና ወይዘሮ ሀዳ አልመሀዲ ልጃቸው የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ታሪካዊ ሁነት መገለጫ በመሆኑ ስሙን "ኮሚሽን" ሲሉ መሰየማቸውንም ገልጸዋል፡፡
የገጠር ሞዴል መንደር አርሶአደሩ ዘመናዊ ሕይወት እንዲመራ አስችሎታል
Jul 26, 2026 144
ቦንጋ ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ የገጠር ሞዴል መንደር አርሶአደሩ ዘመናዊ ሕይወት እንዲመራ አስችሎታል ሲሉ የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር ዙሪያ ጨታ ቀበሌ የተገነባውን የባቾ ገጠር ሞዴል መንደር መርቀው ለተጠቃሚዎች አስረክበዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለፁት፣ ሞዴል የገጠር መንደሩ ለሰውና ለእንስሳት ምቹ መኖሪያን የሚፈጥር፣ የማር፣ የዓሳና ሌሎችም የልማት ስራዎችን ያካተተ ነው ብለዋል። የገጠር ሞዴል መንደሮቹ የሌማት ትሩፋት ስራዎችን ውጤታማ በማድረግ የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ አቅም ለማሳደግ እንደሚያግዙም ተናግረዋል። ዛሬ የተመረቀው የባቾ ሞዴል የገጠር መንደር ይህን ለማሳካት የሚያስችል በመሆኑ ልምዱን ማስፋት ላይ እንደሚሰራ አንስተዋል። የገጠር ሞዴል መንደሩ የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ ናቸው። ባቾ ገጠር ሞዴል መንደር የሌማት ትሩፋትና ዘመናዊ አገልግሎቶችን ያሟላ መሆኑ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ስርዓት የሚቀይር ነው ብለዋል። የአመያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ደጀኔ በበኩላቸው፤ ትኩረት ተነፍጎት የቆየውን የገጠሩ ማህበረሰብ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የገጠር ሞዴል መንደር ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል። የገጠር ሞዴል መንደሩ የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭንና የሶላር፣ የንፁህ የመጠጥ ውሃ እና ሌሎች አገልግሎቶችንም ያካተተ መሆኑን ገልፀዋል። ከግንባታው ተጠቃሚዎች መካከል አቶ ታምሩ ተፈራ እና አቶ ተፈራ ሳካሎ፤ የገጠር ሞዴል መንደሩ ሁሉንም አገልግሎቶች ያሟላ በመሆኑ ዘመናዊ ሕይወት መምራት ያስችለናል ብለዋል። ይህም የገጠሩን ማህበረሰብ የሚያነቃቃና የግብርና ስራዎቹን እንደሚያሳድግም ተናግረዋል።
ለሃገራዊ ምክክር ጉባኤ በተገኙበት የወለዱት እናቶች ጉባኤውን አጠናቀው ወደ መጡበት እስኪመለሱ ድረስ የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ እናደርግላቸዋለን
Jul 26, 2026 115
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ለሃገራዊ ምክክር ጉባኤ በተገኙበት የወለዱት ሁለቱንም አራስ እናቶች ጉባኤውን አጠናቀው ወደ መጡበት እስኪመለሱ ድረስ የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ እናደርግላቸዋለን ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ። ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት፥ ሃዳ አልማህዲ ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ለሃገራዊ ምክክር ከተፎካካሪ ፓርቲ ተወክላ የተጣለባትን ውክላና እና ሃላፊነት በታላቅ የሀገር ፍቅር እና የእኔነት ስሜት እየተወጣች እያለ ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላለች። እኛም ወ/ሮ ሃዳን በአዲስ ዓለማቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ማረፍያ ክፍል አዘጋጅተን ለአራስ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን አሟልተን እንኳን ደስ አለሽ ብለን ጠይቀናታል ብለዋል። ወ/ሮ ሃዳ አልማህዲ በታሪካዊው ሀገራዊ ምክክር ወቅት ላይ የወለደችውን ወንድ ልጅ ኮሚሽን ብላ ስም ማውጣታቸውንም አስታውሰዋል። ወጣቷ የመጣችበትን ታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ለማሳካት ከጥቂት ቀናት እረፍት በኋላ ወደ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እንደምትመለስ መናገሯንም ጠቁመዋል። ከንቲባ አዳነች አክለውም፥ለሃገራዊ ምክክር ጉባኤ በተገኙበት የወለዱት ሁለቱም አራስ እናቶች የመጡበትን ሃገራዊ ምክክር ጉባኤ ያለምንም ችግር አሳክተው እንዲመለሱ ለምክክሩ በቅርበት በሚመቻቸው ቦታ ማረፍያ አዘጋጅተንላቸዋል ነው ያሉት።
ኢኮኖሚ
በክልሉ የአርሶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ ወደ ኢንቨስትመንት ለማሸጋገር የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስመዘገቡ ነው
Jul 26, 2026 131
ደብረ ብርሃን፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የአርሶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ ወደ ኢንቨስትመንት ለማሸጋገር የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ(ዶ/ር) ገለጹ። በሰሜን ሸዋ ዞን በሞረትና ጅሩ ወረዳ የሚገኙ 837 አርሶ አደሮችን ያቀፈው ማህበር “የጅሩ-አግሮ ቢዝነስ“ ኩባንያን ዛሬ መሰረተ። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ(ዶ/ር) በምስረታው ወቅት እንደገለጹት፤ ኩባንያው የአርሶ አደሮችን ምርት በማቀነባበርና እሴት በመጨመር ለገበያ የሚያቀርብ ነው። አርሶ አደሮቹ በማህበር ተደራጅተው የራሳቸውን አግሮ - ቢዝነስ ኩባንያ ማቋቋማቸው ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አርሶ አደሮቹን ከጥሬ ግብአት አቅራቢነት ወደ አምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስተርነት በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል። የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ ደረጀ ማንደፍሮ በበኩላቸው፤ የግብርናውን ምርታማነት በማሳደግ ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የተሰራው ስራ ውጤታማ ሆኗል ብለዋል። የተመሰረተው የቢዝነስ ኩባንያም ውጤታማ የሆኑ አርሶ አደሮችን ምርት በጥሬው ከማቅረብ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ በማቅረብ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል። ኩባንያው የዱቄት ፋብሪካ በማቋቋምና ዱቄት በማምረት በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ፣ ትራክተርና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን ለማስመጣትና በሌሎች የስራ ዘርፎች በመሰማራት ዘርፉን ለማዘመን ያስችላል ብለዋል። በምስረታው ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ጀኔራል ዳይሬክተር ፍሬው ተገኘ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አርሶ አደሮቹ ትራክተርና ሌሎች የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅመው ዘርፉን በማዘመን ውጤታማ እየሆኑ ነው ብለዋል። ኩባንያው መመስረቱም የኢንቨስትመንት ብድር በቀላሉ በማግኘት ፈጥነው የግብርና ምርቶችን በማቀነባበር በከፍተኛ ዋጋ ለሀገር ውስጥና ለውጪ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል። እንደ ሀገር 50 የአግሮ ኢንዱስትሪ ኩባንያ ለመገንባት መታቀዱን ጠቁመው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በዛሬው እለት የተመሰረተው ይህ ኩባንያ አንዱ መሆኑን አመልክተዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተክለየስ በለጠ እንደገለጹት፤ የኩባንያው መመስረት የአርሶ አደሩንና የቤተሰቦቻቸውን ኑሮ ከማሻሻሉም በላይ ፈጣን እድገት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ያበረክታል። የዞኑ አስተዳደርም የተመሰረተው ኩባንያ ውጤታማ ሆኖ ለሌሎች አካባቢዎች ሞዴል እንዲሆን አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
በክልሉ የዜጎችን ጥያቄ የሚመልሱ የልማት ስራዎችን በመተግበር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል
Jul 26, 2026 93
ቦንጋ ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የዜጎችን ጥያቄ የሚመልሱ የልማት ስራዎችን በመተግበር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለፁ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ በ85 ሚሊዮን ብር የተገነባው የኡማ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለፁት፣ የዜጎችን ጥያቄዎች የሚመልሱ ትልልቅ የልማት ስራዎችን በማቀድና ወደ ተግባር በመቀየር የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው። የክልሉ መንግስት ለፕሮጀክቱ ትኩረት በመስጠትና የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ማስቻሉን ተናግረዋል። ድልድዩ አርሶአደሩ በፍራፍሬ እና በእንስሳት ልማት እንዲሁም በእርሻ ስራ ላይ በሰፊው በመሰማራት የኢኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴው ምቹ እንዲሆን ያስችላል ብለዋል፡፡ በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የሕብረተሰቡ ተሳትፎ እያደገ የመጣ በመሆኑ ይህን አጠናክሮ በማስቀጠል የማህበረሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ ተግባራትም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ በበኩላቸው፤ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ 20 የተለያየ ደረጃ ያላቸው ድልድዮች ተገንብተው ወደ ስራ መግባታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ዛሬ የተመረቀው የኡማ ድልድይ ግን በርዝማኔው የመጀመሪያ መሆኑን ገልፀዋል። ከሁለት ዓመት በፊት ግንባታው የተጀመረው የ84 ሜትር ርዝመት ያለው የኡማ ወንዝ ድልድይ ከ85 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበትም ተናግረዋል። የኡማ ወንዝ ሞልቶ በርካታ የልማት ስራዎችንና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን ሲያስተጓጎል መቆየቱን የገለፁት ደግሞ የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ ናቸው። አካባቢው ሰፊ የመልማት አቅም ያለው ነው ያሉት አቶ ታከለ፣ ድልድዩ ይህን ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን የሚያሳልጥ መሆኑን ተናግረዋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ25 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ
Jul 26, 2026 161
አሶሳ፤ ሐምሌ 19/2018 (ኢዜአ)፡- የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት በመጨረሻ ቀን የጉባዔ ውሎው ለ2019 በጀት ዓመት ከ25 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጽድቋል። ለሁለት ቀናት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሲመክር የቆየው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት በዛሬው የመጨረሻ ቀን ውሎው ለ2019 በጀት ዓመት 25 ቢሊዮን 424 ሚሊዮን 655 ሺህ 336 ብር በጀት ነው ያጸደቀው። የረቂቅ በጀቱን ዝርዝር ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ዚያድ አብዱላሂ እንደገለፁት በጀቱ የክልሉን ገቢ የመሰብሰብ አቅም ያገናዘበ እና ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚውል ነው ብለዋል። በጀቱ ለመሠረተ ልማት እና ለትልልቅ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ ትኩረት የሰጠ መሆኑን ገልፀው፥ በየደረጃው የሚገኙ አስፈጻሚ አካላትም በጀቱን ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው አስታውቀዋል። በክልሉ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱ እየተሻሻለ በመምጣቱ ከዘንድሮ በጀት 61 ነጥብ 5 በመቶ የሚሆነው በክልሉ የውስጥ ገቢ የሚሸፈን መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል። በረቂቅ በጀቱ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የምክርቤት አባላትም በጀቱን በቁጠባ እና በአግባቡ ተግባር ላይ በማዋል የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን በፍትሃዊነት መፈጸም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ምክርቤቱ በተጨማሪም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት የተሻሻለ የገቢ ግብር ለመወሰን የወጣ ረቂቅ አዋጅን እና የክልሉን የፋይናንስ አስተዳደርን ለማሻሻል የወጣ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቋል።
በምዕራብ ሸዋ ዞን ከ133 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ እድል ተፈጥሯል
Jul 26, 2026 132
አምቦ ፤ ሐምሌ 19/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ 133 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን የዞኑ የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። መንግስት በሀገሪቱ የሚታየውን የወጣቶች የሥራ አጥነት ቁጥር ለመቀነስ እና ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የክህሎት ልማት ዘርፍን በትኩረት እየሰራበት ይገኛል። በተለይም በክልሎች በሚገኙ የተለያዩ ዞኖች የወጣቶችን አቅም በማሳደግ እና በየአካባቢው የሚገኙ የኢኮኖሚ አማራጮችን በማስፋት በርካቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል። በምዕራብ ሸዋ ዞንም በአካባቢው የሚገኙ የወጣቶችን የሥራ አጥነት ችግር ለማቃለል ባለፉት የበጀት ዓመታት በርካታ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። ዞኑ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ምቹ የሆኑ የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ያሉት ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል ግብርና እና የግብርና እሴት መጨመር፣ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች፣ የአገልግሎት ዘርፍ እና ንግድ ተጠቃሽ ናቸው። የምዕራብ ሸዋ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ የኔነሽ ምስጋና ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በ2018 በጀት ዓመት በዞኑ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም ከማሳደግ ባለፈ በአገር እድገት ውስጥ የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ ለማስቻል የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል። በዚህም በዞኑ በከተማና በገጠር አካባቢዎች ለ129 ሺህ 132 ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ፣ ከ133 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል። የስራ እድሉ የተፈጠረው፣ በግብርና፣ በአገልግሎት፤ በእንጨትና ብረታ ብረት፤ የወተት ላምና የዶሮ እርባታ፣ የከብቶች ማድለብን ጨምሮ ሌሎች የሥራ ዘርፎች መሆናቸውን ገልፀዋል። ወጣቶቹ በሥራቸው ስኬታማ እንዲሆኑም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ከመስጠት ባለፈ የብድር አቅርቦት፣ የመሥሪያና የመሸጫ ቦታዎች የማመቻቸት ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በዚህ መሰረት በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ብድር፣ ከ218 በላይ ሼዶችና ኮንቴይነሮች፣ 140 የሥራ ዘርፍ ክላስተሮች እንዲሁም 5 ሺህ 903 ሄክታር መሬት መቅረቡን ጠቁመዋል። ይህንን ተግባር አጠናክሮ በማስቀጠል በአዲሱ በጀት ዓመትም በርካታ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ አዳዲስ የሥራ ዘርፎችን ለመፍጠር አቅደው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ የሥራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች በበኩላቸው፤ ከመንግስት የተመቻቸላቸውን የብድር ድጋፍ እና የመስሪያ ቦታ በመጠቀም፣ በትጋትና በጥንካሬ በመስራት አሁን ላይ አርአያ የሚሆን ውጤት በማስመዝገብ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ወጣት ጫላ አያና፤ በቶኬ ኩታዬ ወረዳ 'የጫላና ብርቱካን የእንጨትና ብረታ ብረት ስራ' በተሰኘው ማህበር በመደራጀት ከመንግስት ባገኙት 200 ሺህ ብርና ቦታ ተግተው በመስራት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግሯል። በስራው የስራ እድል መፍጠር መቻላቸውን ጠቅሶ፣ እንዲሁም 100 ሺህ ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘታቸውን አክሏል። ሌላው ወጣት አብዲ ተስፋዬ እንደገለጸው፤ በተመቻቸላቸው ዕድል በመጠቀም ባገኙት 2 ሚሊዮን ብር ካፒታል መነሻነት ከጓደኞቹ ጋር በመደራጀት በወተት ላም እርባታ ላይ ተሰማርተው እየሰሩ ነው። ሥራውን በ10 ላሞች እንደጀመሩና በዚህም የራሳቸውንም ሆነ የቤተሰቦቻቸውን ሕይወት በተሻለ ሁኔታ እየመሩ እንደሚገኙ ተናግሯል። ከዩኒቨርሲቲ በድግሪ ከተመረቀ በኋላ ለሁለት ዓመታት ያለ ምንም ስራ ቤተሰቦቹ ላይ ጥገኛ ሆኖ መቆየቱን አስታውሶ፣ በአሁኑ ወቅት መንግስት ባመቻቸላቸው ምቹ ሁኔታን በመጠቀም ተደራጅቶ በመስራቱ ከራሱም አልፎ በኢኮኖሚው እድገት ውስጥ የራሱን ሚና ለመወጣት ማቀዱን አመልክቷል። በ'ብርሃኑ ኩማላ እና ጎደኞቹ' በተሰኘው ማህበር በዶሮ እርባታ በመደራጀት በተሰጣቸው 300ሺህ ብር ብድር 800 እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማስገባት ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን የተናገረው ደግሞ ወጣት ሱፋና አለሙ ነው፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ጋር በመተባበር ያስገነባው ዘመናዊ የላቀ ላቦራቶሪ የሀገራቱን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያሳይ ነው
Jul 26, 2026 129
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ጋር በመተባበር ያስገነባው ዘመናዊ የላቀ ላቦራቶሪ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ መሸጋገሩን የሚያሳይ ነው ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሯ ኢንጅነር አይሻ መሀመድ ገለጹ። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ጋር በመተባበር ያስገነባውን የማሰልጠኛ እና የምርምር ዘመናዊ የላቀ ላብራቶሪ ስራ አስጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሀግብሩ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ፤የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ፣የመከላከያ ሰራዊት ጀነራል መኮንኖች፣የተባበሩት አረብ ኢመሬትስ ተወካዮች እንዲሁም የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። ላቦራቶሪው በ20 ሺህ 850 ካሬ ሜትር መሬት ላይ የተገነባ ሲሆን በውስጡ ለስልጠና እና ምርምር የሚያገለግሉ ቁሳቁሶች የተሟሉለት መሆኑ ተገልጿል። ላቦራቶሪው በውስጡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የሳይበር፣ የኤሌክትሪክ ሀይል፣የአውቶሜሽን፣የኮሙኒኬሽን እና ኤሌክትሮኒክስ፣የነርሲንግ ሲሙሌሽን ላብራቶሪዎች በውስጡ ማካተቱ ተመላክቷል። በተጨማሪም ላቦራቶሪው ዘመናዊ የሶላር ስርዓት እና ዘመናዊ መሳሪያዎች የተገጠሙለት መሆኑ ተመላክቷል። የመከላከያ ሚኒስትሯ ኢንጅነር አይሻ መሀመድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በላቦራቶሪው መሰረተ ልማቱ የረቀቁ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ ማዋል ብቻውን በቂ አይደለም ብለዋል። ይልቁንም እውቀትን ወደ ሙያዊ ብቃት፣ምርምርን ወደ ፈጠራ እንዲሁም ፈጠራን ለሀገራችን አገልግሎት ወደሚውሉ ተግባራዊ መፍትሄዎች የሚቀይር አዲስ የትምህርት የሳይንስ እና ተቋማዊ አቅም የተከፈተበት ታላቅ አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል። የዚህ የልህቀት ምእራፍ መሰረት በኢትዮጵያ እና በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች መካከል ዘመናትን የተሻገረ ወዳጅነት እና ስትራቴጂካዊ አጋርነት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ታሪካዊ ወዳጅነት ቀደም ሲል ከነበሩት ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር አሁን ላይ የሁለቱን ሀገራት ሀገራዊ ደህንነት፣ቴክኖሎጂያዊ ሽግግርና የተቋማትን ዘመናዊነት ወደሚያጎለብት የላቀ ምእራፍ መሸጋገሩን ጠቁመዋል። የላቦራቶሪ ማእከሉ በቁሳቁስ ድጋፍ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በእውቀት ሽግግር ፣በሳይንሳዊ ምርምር እና በሀገር በቀል የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ትውልድን የሚቀርጽ መሆኑን ጠቁመዋል። ላቦራቶሪው የመከላከያ ሰራዊቱን ሁለንተናዊ የዘመናዊነት ጉዞ የሚያፋጥን የተቋሙን የቴክኖሎጂና ምርምር መሰረት የሚያጎለብት እና የወደፊት ሀገራዊ ደህንነት በጽኑ መሰረት ላይ የሚጥል ታላቅ እርምጃ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግስት ጋር በመተባበር ያስገነባው ዘመናዊ የላቀ ላቦራቶሪ የሀገራቱን ዘላቂ ወዳጅነት የሚያሳይ ታሪካዊ ምልክት ነው
Jul 26, 2026 128
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግስት ጋር በመተባበር ያስገነባው ዘመናዊ የላቀ ላቦራቶሪ የሀገራቱን ዘላቂ ወዳጅነት እና ስትራቴጂያዊ አጋርነትን የሚያሳይ ታሪካዊ ምልክት መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ ገለጹ። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግስት ጋር በመተባበር ያስገነባውን የማሰልጠኛ እና የምርምር ዘመናዊ የላቀ ላቦራቶሪ ስራ አስጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሀግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጅነር አይሻ መሀመድ፣ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)፣የመከላከያ ሰራዊት ጄኔራል መኮንኖች፣የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ተወካዮች እንዲሁም የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። ላቦራቶሪው በ20 ሺህ 850 ካሬ ሜትር ላይ የተገነባ ሲሆን በውስጡ ለስልጠና እና ምርምር የሚያገለግሉ ቁሳቁሶች የተሟሉለት መሆኑ ተገልጿል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ፕሮጀክቱ በእውቀት፣ በፈጠራና በሰው ኃብት ላይ የሚደረግ ኢንቨስትመንት ለዘላቂ ልማትና ለብሔራዊ ደህንነት መሠረት መሆኑን የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። ለፕሮጀክቱ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱት የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግሥት ላሳየው ድጋፍና ቁርጠኝነት ምስጋና አቅርበዋል። ይህም በሁለቱ ወንድማማች ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ግንኙነትና የጋራ የልማት ራዕይ የሚያሳይ ተጨማሪ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ላቦራቶሪው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የሳይበር ደህንነት፣ የመገናኛ ምህንድስና፣ የአውቶሜሽንና የቁጥጥር ሥርዓቶች፣ የኃይል ምህንድስና፣ የ3ዲ ዲዛይን፣ የፕሮቶታይፕ ልማት እና የነርሲንግ ሲሙሌሽን ዘርፎችን የሚያካትቱ ዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው መገልገያዎችን መያዙን ተናግረዋል። ይህም ለከፍተኛ ትምህርት፣ ለሳይንሳዊ ምርምር፣ ለቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ ለምርት ልማት፣ ለምህንድስና መፍትሔዎችና ለቴክኖሎጂ ሽግግር የተቀናጀ መድረክ እንደሚፈጥር አንስተዋል። በተጨማሪም ማዕከሉ በዩኒቨርሲቲዎች፣ በኢንዱስትሪ፣በመንግሥት ተቋማትና በዓለም አቀፍ አጋሮች መካከል የምርምርና የፈጠራ ትብብርን የሚያጠናክር መሆኑን ጠቁመዋል። የማዕከሉ ስኬት በተገጠሙ መሣሪያዎች ሳይሆን በሚያፈራቸው ብቁ ባለሙያዎች፣ በሚያመነጨው ምርምር፣ በሚፈጥረው ፈጠራና ለሀገር የሚያበረክተው ተጨባጭ አስተዋጽኦ እንደሚለካ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የማሰልጠኛ እና የምርምር የላቀ ላቦራቶሪ በይፋ ስራ ጀመረ
Jul 26, 2026 117
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከተባበሩት አረብ ኢምሬቶች (UAE) መንግስት ጋር በመተባበር ያስገነባውን ዘመናዊ የማሰልጠኛ እና የምርምር የላቀ ላቦራቶሪ በይፋ ስራ አስጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጅነር አይሻ መሐመድ፣ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ፣ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ጀነራል መኮንኖች፣ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ተወካዮች እንዲሁም የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል። ላቦራቶሪው በ20 ሺህ 850 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሲሆን፣ ለላቀ ስልጠና እና ምርምር የሚያስፈልጉ ዘመናዊ ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ የተሟሉለት ነው። በውስጡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣የሳይበር፣የኤሌክትሪክ ኃይል፣የአውቶሜሽን፣ የኮሙኒኬሽን እና ኤሌክትሮኒክስ እንዲሁም የነርሲንግ ሲሙሌሽን ላቦራቶሪዎችን አካቷል። ህንፃዎች በተለየ መልኩ ዘመናዊ የሶላር የኃይል ስርዓትና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙለት ነው። ማዕከሉ የተለያዩ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ እና የመከላከያ ምርምር ዘርፎችን በአንድ ላይ የሚያገናኝ ዘመናዊ የእውቀት ማዕከል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ ለዩኒቨርሲቲው ወደ ተግባራዊ ምርምርና ፈጠራ ይበልጥ ለመሸጋገር ትልቅ እምርታን የሚፈጥር ነው ተብሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ማዕከሉ ለመከላከያ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን ለሀገሪቱ አጠቃላይ የቴክኖሎጂ፣ የኢንዱስትሪ፣የጤና እና የሳይንስ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተመላክቷል።
በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ የዲጂታል ሽግግርን የሚያፋጥን የሰው ኃይል እየተገነባ ነው
Jul 25, 2026 371
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ የዲጂታል ሽግግርን የሚያፋጥን የሰው ኃይል እየተገነባ መሆኑን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለመጀመሪያ ጊዜ በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሰለጠኑ ስታርት አፖችን አስመርቋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ዲጂታል ሽግግር ጠንካራ የሰው ኃይል አቅም እንዲሁም አስተማማኝ መሠረተ ልማቶችን ይጠይቃል። ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሀገሪቱን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ በአፍሪካ የመጀመሪያው የሰው ሠራሽ አስተውሎት ፖሊሲና ስትራቴጂ መቀረጹን፣ ችግር ፈቺ ውጤቶች መመረታቸውን፣ ለአለም ገበያ ብቁ የሆኑ ዲጂታል ባለሙያዎችን ማፍራት መቻሉን፣ የሰው ሠራሽ አስተውሎት መሠረተ ልማት ዝርጋታና ሌሎች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰዋል። በሁሉም ዘርፎች በተለይም ቅድሚያ በሚሰጣቸው የፍትህና አስተዳደር፣ ስማርት ኮርት (ዘመናዊ ፍርድ ቤት)ና ስማርት ፖሊስ ጣቢያ፣ ጤና፣ የሕዝብ አገልግሎትና በሌሎች ዘርፎች በAI የታገዙ ቴክኖሎጂዎች በስፋት ሥራ ላይ መዋላቸውን ገልጸዋል። በዘርፉ ለተገኘው ስኬት በስታርታፕ፣ ሰመር ካምፕ፣ በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና በሌሎች ተቋማት የሰው ኃይል ልማት ጠንካራ የአቅም ግንባታ ሥራዎች በመከናወኑ ነው ብለዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሰለጠኑት ተመራቂዎች የዲጂታል ኢኮኖሚውን ለማንቀሳቀስ ዝግጁ የሆኑ፣ የተፈተሹ፣ ሥራ ላይ የዋሉና በገበያው ሊስፋፉ የሚችሉ ውጤቶች ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እነዚህ ውጤቶች የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ወደ ተግባር መሸጋገሩን እንደሚያሳዩ ተናግረዋል። በዕለቱ በተዘጋጀው አውደ-ርዕይ ሰልጣኞቹ በጤና፣ በትምህርት፣ በትራንስፖርት፣ በቋንቋ ቴክኖሎጂ፣ በስማርት ሲቲ፣ በፋይናንስ እና በሰብዓዊ ልማት ዘርፎች የሠሯቸውን ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለዕይታ አቅርበዋል።
ስፖርት
ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በስፖርት መሰረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ መስራት ይገባል
Jul 26, 2026 102
ሀዋሳ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እግር ኳስ ተወዳዳሪና ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በስፖርት መሠረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ የሚሰሩ ስራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተጠቆመ። እ.አ.አ. በ1957 የተመሰረተው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መስራች ከነበሩ ሀገራት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እግር ኳስ ዕድገት ትልቅ አሻራ አሳርፋለች። የአፍሪካ እግር ኳስ በዓለም መድረክ የሚገባውን ቦታ እንዲይዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉት የካፍ ፕሬዝዳንት የነበሩት የይድነቃቸው ተሰማ ሀገር ኢትዮጵያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የእግር ኳስ አፍቃሪያን ያሉባትም ናት። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እግር ኳስ ዕድገት ያኖረችውን አሻራና የቀደመ ገናና ታሪክ በማንሳት የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ጥያቄ ማቅረቧም ይታወቃል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ዋና አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ እና የክለቡ ተጫዋች ሁሴን ጠሃ፤ በኢትዮጵያ ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በመሰረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ በእግር ኳሱ የላቀ ችሎታ ያላቸው ተጫዋቾች እንዳሏት አንስተው ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት ዕድሎችን ለመጠቀም ብዙ ልንሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። የ2018ቱ የሲቢኢ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው ቡድን አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ እንደገለጸው፤ ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት ሌላው ዓለም የሚሰራውን መስራት መቻል አለብን ። የስፖርት መሰረተ ልማትና የታዳጊ ስልጠና ማዕከላትን ማጠናከር፤ የምልመላ ስርዓትና የውድድር ዕድሎችን ማስፋት ቀዳሚዎች መሆናቸውን አንስቷል። ዕምቅ ችሎታ ያላቸው ተጫዋቾች የሚፈሩባቸው ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የሚደረጉ ስልጠናዎችና ውድድሮች ላይ ማተኮር እንደሚገባም አክሏል። አሰልጣኞችን ልምድ ባላቸው ሀገራት ማስተማር፣ ወጥ የሆነ የስልጠና ማኑዋል ማዘጋጀትና ሳይንሳዊ የሆነ የምልመላ ስርዓት መዘርጋት ሌላው ሊተኮርበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አንስቷል። መንግስት የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ጥያቄ ማቅረቡ በስፖርቱ ዘርፍ ከፍተኛ የሆነ መነሳሳትን እንደሚፈጥር የጠቀሰው አሰልጣኝ ያሬድ ዕድሉን መጠቀም ይገባናል ሲል ገልጿል። ለዋናው ብሔራዊ ቡድን የመጫወት ህልም ይዞ እየሰራ ያለው የክለቡ ከ20 ዓመት በታች የግራ መስመር አጥቂ ሁሴን ጠሃ በበኩሉ፤ ተፎካካሪ ብሔራዊ ቡድን ለመፍጠር ታዳጊዎችና የስልጠና ሜዳዎች ሊጠናከሩ ይገባል ነው ያለው።
የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
Jul 24, 2026 210
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን የርገን ክሎፕን የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የ59 ዓመቱ ጀርመናዊ የአራት ዓመት ውል የተፈራረሙ ሲሆን ስምምነቱ አሰልጣኙን እስከ 2030 የዓለም ዋንጫ መጨረሻ ድረስ የሚያቆያቸው ነው። ክሎፕ በቦታው የተኩት በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ጀርመን በ32ቱ ዙር በፓራጓይ ተሸንፋ ከውድድሩ ውጪ ከሆነች በኋላ ከኃላፊነታቸው የለቀቁትን ጁሊያን ናጌልስማንን በመተካት ነው። ከሊቨርፑል የዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ የሬድ ቡል ሳልስበርግ የዓለም እግር ኳስ ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት ክሎፕ፣ የጀርመን እግር ኳስን እንደገና ወደ ቀደመ ገናናነቱ የመመለስ ትልቅ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ክሎፕ ከጀርመን ብሔራዊ ቡድን ጋር የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም. በዩኤፋ ኔሽንስ ሊግ (Uefa Nations League) ከኔዘርላንድስ ጋር ያደርጋሉ።
የዓለም አትሌቲክስ የአትሌት ትዕግስት አሰፋ የሴቶች ብቻ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን አፀደቀ
Jul 23, 2026 228
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም አትሌቲክስ የኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ የሴቶች ብቻ (women’s only) የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን ዛሬ ማፅደቁን ይፋ አድርጓል። አትሌት ትዕግስት እ.አ.አ አፕሪል 26 / 2026 በለንደን ማራቶን 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ከ41 ሴኮንድ በመግባት እ.አ.አ በ2025 በራሷ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን በዘጠኝ ሴኮንድ በማሻሻል አሸንፋለች። የዓለም አትሌቲክስ የአትሌቷን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረ ወሰን ዛሬ ማፅደቁን አስታውቋል። የሴቶች ብቻ (women’s only) የዓለም ክብረ ወሰን ሴቶች ብቻ በሮጡበት ውድድር ብቻ የተመዘገበ የዓለም ፈጣን ሰዓት ማለት ነው። የዚህ የዓለም ክብረ ወሰን አመዘጋገብ በሴቶች ውድድር ላይ የወንድ አሯሯጮች ወይም ወንዶች ተቀላቅለው ሲሮጡ (አጠቃላይ ሩጫ) ከሚመዘገበው የዓለም ክብረ ወሰን ጋር የሚለያይ ነው። ወንዶች በሴቶች ውድድር ላይ መኖራቸው የውድድሩን አዝማሚያ እና ሴቶች የሚያስመዘግቡት ሰዓት ላይ ተጽእኖ እንደሚያሳድር የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል። ሴት እና ወንድ ተደባልቀው በሚሮጡበት አጠቃላይ የሴቶች ማራቶን ውድድር የዓለም ክብረ ወሰንን (Overall women's world record) የያዘችው ኬንያዊቷ አትሌት ሩት ቼፕጌቲች ናት። ሩት እ.አ.አ በ2024 በቺካጎ ማራቶን 2 ሰዓት ከ9 ደቂቃ ከ56 ሴኮንድ በመግባት ክብረ ወሰኑን ጨብጣለች። የዓለም አትሌቲክስ ከአትሌት ትዕግስት በተጨማሪ ሰባት የዓለም ክብረ ወሰኖችን ማጽደቁን አስታውቋል። እውቅናና ፈቃድ በተሰጣቸው ውድድሮች ላይ ማሸነፍ፣ የውድድር ሜዳዎቹ የሚፈለገውን መስፈርት ያሟሉ መሆንና አትሌቶች በአበረታች ቅመም ምርምራ ውጤት ጤነኛ መሆናቸው መረጋገጥ አትሌቶች የዓለም ክብረ-ወሰን ባለቤት የሚሆኑባቸው ዋነኛ ቅደመ-ሁኔታዎች ናቸው።
የስፔኑ ሮድሪ የዓለም ዋንጫው ኮከብ ተጫዋች ሆኖ ተመረጠ
Jul 20, 2026 644
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ተጠናቋል። በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ ዋንጫውን አንስታለች። ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ የኮከብ ተጫዋቾች ሽልማት ስነ ስርዓት ተካሂዷል። በዚሁ መሰረት የስፔኑ አምበል ሮድሪ የዓለም ዋንጫው ኮከብ ተጫዋች በመባል ተመርጧል። የስፔኑ ተከላካይ ፓዎ ኩባርሲ የወጣት ኮከብ ተጫዋች ሽልማትን አግኝቷል። ኡናይ ሲሞን (ስፔን ) የውድድሩ ኮከብ ግብ ጠባቂ ሆኗል። ፈረንሳዊው ኪሊያን እምባፔ 10 ግቦች በማስቆጠር የኮከብ ግብ አግቢነቱን ሽልማት ወስዷል።
አካባቢ ጥበቃ
ፅዱና አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ ነው
Jul 26, 2026 129
ሰመራ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ ፅዱና አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተጀመሩ የጽዳትና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ውጤታማ እየሆኑ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ገለጸ። ሦስተኛው ዙር ክልል አቀፍ የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ መድረክ "ፅዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ" በሚል መሪ ሐሳብ በሰመራ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ (ዶ/ር)፤ 3ኛው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በቀጣይ ሶስት ወራት የሚተገበር መሆኑን ጠቅሰዋል። በንቅናቄው በዋናነት የፕላስቲክ ብክለትን መከላከል፣ የአደገኛ ኬሚካሎችና ቆሻሻዎች አያያዝ፣ እንዲሁም የድምፅ ብክለትን መቀነስ ላይ ትኩረት አድርጎ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። እነዚህ የተከናወኑ ተግባራትም ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆናቸው ጠቁመው፤ ይህንን ግብ ለማሳካት የሕግ አፈጻጸምን ማጠናከር፣ የተቋማትን ቅንጅት ማሻሻል፣ የማህበረሰብ ተሳትፎ ማሳደግ፣ የመልሶ መጠቀም ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ እንዲሁም የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ማጎልበት ዋና ትኩረቶቻችን ይሆናሉ ብለዋል። ፅዱና አረንጓዴ ኢትዮጵያ በመንግስት ብቻ አይተገበርም ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ በየቤታችን፣ በየትምህርት ቤቶቻችን፣ በየመሥሪያ ቤቶቻችን፣ በየፋብሪካዎችና በየማህበረሰባችን በሚፈፀሙ ተደማሪ ተግባራት አቅም ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። ምድራችን በአየር ንብረት ለውጥ፣ በብዝሃ ሕይወት መመናመን እና በአካባቢ ብክለት እጅጉን እየተፈተነች መሆኑን ገልፀው፤ በዚህም ምክንያት በተለይም የፕላስቲክ ብክለት በፍጥነት በመጨመሩ ምክንያት በወንዞች፣ በአፈርና በሰው ጤና ላይ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን ተናግረዋል። የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ኬሚካሎችና በአደገኛ ቆሻሻዎች ያልተገባ አያያዝ እንዲሁም በከተሞች እየጨመረ የመጣው የድምፅ ብክለት በሰው ጤና፣ በኢኮኖሚ እና በአካባቢ ደህንነት ላይ ከባድ ተፅዕኖ ማሳደራቸውንም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ በበርካታ ፖሊሲና በፕሮግራሞች የተደገፈ ስትራቴጂያዊ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑንም በመድረኩ አብራርተዋል። በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት እየተተገበሩ ያሉ የአረንጓዴ አሻራ፣ የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ ልማት፣ የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ልማት ስራዎች ሁነኛ ማሳያዎች መሆናቸውን አንስተዋል። በመሆኑም ፅዱና አረንጓዴ ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ ሁሉም የመንግስት ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የሴቶችና የወጣቶች ማህበራት እንዲሁም እያንዳንዱ ዜጋ የዚህ ሀገራዊ ንቅናቄ ባለቤት በመሆን በንቃት ተሳትፎውን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል። የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት አስተዳደር ቢሮ ኀላፊ አቶ ኡመር ኑር፤ ፅዱና አረንጓዴ ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግና አስተማሪ የሆኑ እርምጃዎችን በመውሰድ ለተግባራዊነቱ በየደረጃው የሚገኝ አመራር ኀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የክልሉ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዶ ሃመሎ በበኩላቸው፤ በክልሉ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ የቆሻሻ አያያዝን በማሻሻል፣ የፕላስቲክ ብክለትን በመቆጣጠር፣ የብዝሃ ሕይወትን በመጠበቅና የአካባቢ ሕጎችን በማስፈጸም ላይ መሆናቸውን አንስተዋል። ለዘላቂነቱም የማኅበረሰቡን የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ በማሳደግና ከፌዴራል መንግሥት፣ ከክልሎች፣ ከልማት አጋሮች እና ከማኅበረሰቡ ጋር በመተባበር የሚታይ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በንቅናቄው መድረክ ላይ የአፋር ክልል ከፍተኛ የስራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የአካባቢ ሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና አለው
Jul 26, 2026 112
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/ 2018 (ኢዜአ):- የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የአካባቢ ሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና እንዳለው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ስትራቴጂክ እና ከፍተኛ አመራሮች በብሔራዊ ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ችግኝ በመትከል እንደ ተቋም የሚከናወነውን ዓመታዊ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ መርሐ-ግብር በይፋ ጀምረዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት እንደ ሀገር የተካሄዱት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብሮች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ይገኛሉ፡፡ የሀገራችንን የተራቆተ መሬት በተለያዩ ተክሎች በማልበስ የደን ሽፋንን ማሳደግ መቻሉን ያነሱት አምባሳደር ሬድዋን፤ እየተተከሉ ያሉ ችግኞችን ውጤት መመልከት እና ማጣጣም መቻሉን አመልክተዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጄነራል አሰፋ አብዩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በአካባቢ ሥነ-ምኅዳር ላይ የሚፈጸሙ ውድመቶች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የማኅበረሰብን ደኅንነት አደጋ ላይ እንደሚጥሉ ጠቁመዋል፡፡ በሥነ- ምኅዳር መራቆት ምክንያት የሚከሰት የዝናብ እጥረት፣ የመሬት መሸርሸርና ድርቅ ምርታማነትን በመቀነስ ሕዝቦችን ለምግብ እጥረትና ለፍልሰት በመዳረግ ብሔራዊ ደኅንነትን አደጋ ውስጥ ይከታል ብለዋል፡፡ በመሆኑም በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብሮች እየተከናወኑ ያሉ የተፈጥሮ እንክብካቤ እና የልማት ስራዎች እንደ አንድ ብሔራዊ ደኅንነትን የማረጋገጥ ስምሪት ተደርገው ይወሰዳሉ ብለዋል፡፡ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ሁሉንም ሠራተኞች ባሳተፈ መልኩ ችግኝ የመትከል መርሐ-ግብሩን ለማከናወን ዝግጅት አድርጓል ነው ያሉት፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙኃን የላከው መረጃ እንዳመለከተው፤ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተካሄዱ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብሮች በአጠቃላይ ከ307 ሺ በላይ የዛፍ፣ የፍራፍሬ እና የውበት ዛፍ ችግኞችን በማዘጋጀት እና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ እንዲተከሉ አድርጓል፡
በክልሉ ለአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ስኬታማነት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል - ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ
Jul 25, 2026 155
ጋምቤላ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ እየተካሄደ ላለው የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ስኬታማነት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። ''ተስፋን እንትከል'' በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ የ2018 የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ማስጀመሪያ ስነ ስርአት በማጃንግ ዞን በመንገሺ ወረዳ ተካሂዷል። ርዕሰ መስተዳድሯ በወቅቱ እንዳሉት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎችን በማጠናከር ለግብርና ልማቱ ስኬታማነት ልንተጋ ይገባል። በክልሉ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን ለማረጋገጥ ባለፉት አመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ስራዎች በርካታ ስኬቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት በተከናወኑት የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት በርካታ የተራቆቱ አካባቢዎች ከማገገማቸው ባለፈ የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻሉን ገልፀዋል። በቀጣይም የተጀመረውን ልማት በማሳለጥ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ መሳካት ያላሰለሰ ጥረት ልናደርግ ይገባል ብለዋል። በዘንድሮው ዓመት እየተከናወነ ላለው የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት የክልሉ ህዝብ ተሳትፎና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሯ አሳስበዋል። የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኡጁሉ ኡሞድ በበኩላቸው እንደገለጹት የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት በመቀነስና የአፈር ለምነትን በመጨመር የአርሶና አርብቶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ ረገድ የማይተካ ሚና አበርክቷል። በክልሉ ባለፉት አመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ከ50 ሺህ ሄክታር በላይ የተራቆተ መሬት በደን መሸፈኑን ጠቅሰዋል። በአረንጓዴ ሻራ ልማት የለሙ የፍራፍሬና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በህብረተሰቡ ህይወት ላይ አወንታዊ ለውጥ እያመጡ መሆናቸውን ገልፀዋል። ዘንድሮም ከሚተከሉ ችግኞች መካከል 60 በመቶ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ትሩፋትና የሕብረብሔራዊ አንድነት የልማት ምልክት ነው
Jul 25, 2026 371
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ትሩፋትና የሕብረብሔራዊ አንድነት የልማት ምልክት መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርአት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) አመራር አባላት በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ ''ተስፋን እንትከል'' በሚል መሪ ሃሳብ የአረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትርና የኢዜአ ቦርድ ሰብሳቢ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ አረንጓዴ ዐሻራ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስምና ዝና ከፍ እያደረገ የሚገኝ ሀገራዊ ተነሳሽነት ነው። በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በኢትዮጵያ በርካታ ቢሊየን ችግኞች መተከላቸው ሀገር ወደ አረንጓዴ ኢኮኖሚ የምታደርገው ሽግግር እየሰመረ መሆኑን በተግባር እንደሚያሳይ ገልጸዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ከሀገር ውስጥ የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ባሻገር በቀጣናዊ ትብብር ውስጥም አዲስ የዲፕሎማሲ መልዕክት እያስተላለፈ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ችግኝ በማቅረብና የአካባቢ ጥበቃ ተሞክሮዎችን በማካፈል ቀጣናዊ ትስስርን እያጠናከረች ነው፤ ይህም በርካታ የዲፕሎማሲ ትሩፋቶችን እያስገኘ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የወሰድነው ተግባራዊ እርምጃ ዓለም እንደ ተሞክሮ እየተመለከተው መሆኑንም ጠቅሰዋል። ይህም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ዕውቅናና አድናቆት እንድታገኝ እንዳስቻላት አብራርተዋል። በሀገር ውስጥም አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎችን የጋራ ተሳትፎ በማሳደግ ኃይማኖት፣ ዕድሜና ጾታ ሳይገድባቸው ኢትዮጵያውያንን በአንድ ዓላማ ያሰባሰበ ሀገራዊ የልማት አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። መርሃ ግብሩ በሀገር ጉዳይ በጋራ መሥራት ያለውን ጠቀሜታ ያሳየና ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ መሆኑን ጠቅሰዋል። ከኢኮኖሚ አኳያም አረንጓዴ ዐሻራ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የገጠርና የከተማ ኢኮኖሚን ለማጠናከር እንዲሁም በቤተሰብ ደረጃ የተሻለ ኑሮ ለመፍጠር አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ ኢዜአ እንደ ተቋም በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። በቢሾፍቱ ከተማ የተካሄደው የችግኝ ተከላም በዚህ ክረምት ኢዜአ ያካሄደው ሁለተኛው የአረንጓዴ ዐሻራ ተግባር ሲሆን፤ በቀጣይም በክልሎች የተለያዩ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሮችን እንደሚያካሂድ ገልጸዋል። ኢዜአ ዜጎች በአረንጓዴ ዐሻራ ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የማስገንዘብና የማንቃት ሥራውን በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 20416
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 13253
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 12044
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 11945
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የባሕር በር ፣ የኢትዮጵያውያን የልማትና የሕልውና ጥያቄ
Jul 26, 2026 109
የባሕር በር ፣ የኢትዮጵያውያን የልማትና የሕልውና ጥያቄ በዜናው ፈንቴ እንደ መግቢያ፡- የባሕር በር የአንድ ሀገር የውኃ ዳርቻ ባለቤትነት መገለጫ ብቻ አይደለም፤ የንግድ ደም ስር፣ የኢኮኖሚ አምድ፣ ፍኖተ ስልጣኔ፣ የባህል መስተጋብርና የጂኦፖለቲካ ኃይል እንጂ። የዓለም ታላላቅ የሥልጣኔ መሰረት የሆኑ ከተሞች የውኃማ አካላትን ጠርዝ ተንተርሰው የተቆረቆሩ ናቸው። ባሕር የውሃ ስፋት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ የንግድ ማሳለጫ፣ የደህንነት ዋስትና የሉዓላዊነት ማረጋገጫ ነው። የዓለም 80 በመቶ የንግድ ልውውጥ በባህር ላይ ይከወናል፤ በዓመቱ በአማካኝ እስከ 12 ቢሊዮን ቶን ጭነት ይጓጓዛል፤ የባሕር በር ያላቸው ሀገራት በፈጣን ዕድገት፣ በወጭ ንግድ፣ በኢንዱስትሪ መስፋፋትና በቀጣናዊ ተፅዕኖ የተሻለ አቅም መገንባት ይችላሉ፤ የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት ደግሞ ለከፍተኛ የሎጂስቲክስ ወጪ፣ ለንግድ መጓተትና ለውጭ ጥገኝነትን ይጋለጣሉ፡፡ ለዚህም ነው የባሕር በር የአንድ ሀገርና ዜጎች የህልውና ጉዳይ ነው የሚባለው። ይህ እውነታ በኢትዮጵያ በግልጽ ይንጸባረቃል፤ በአፍሪካ ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ያላት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ በኃይል ልማትና በዲጂታል ኢኮኖሚ እየተለወጠች ነገር ግን የባሕር በር የሌላት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት። ተለዋዋጭ በሆነው የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ትልቅ የሕዝብ ቁጥርና በፍጥነት እያደገ ያለ ኢኮኖሚ ለምትመራው ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባሕር በር ማግኘት የህልውና ፍትሕ እንጂ ቅንጦት አይደለም፡፡ ለቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ልማትም ዋስትና። ቀይ ባሕር አውሮፓን፣ ኤዥያና አፍሪካን የሚያገናኝ፤ የስዌዝ ቦይን ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር የሚያስተሳስር፣ የዓለምን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያሳልጥ የዓለም ወሳኝ የባሕር መስመር ነው። በዚህ ወሳኝ ጂኦ ስትራቴጂክ ቀጣና የሚገኝ ሀገር አስተማማኝ የባሕር በር ያስፈልገዋል። ኢትዮጵያም ይገባታል፤ የታሪክ፣ የጂኦግራፊ፣ ነባራዊ ሁኔታና የተፈጥሮ ሚዛን ወደ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ያጋደለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ለሺህ ዘመናት የተሻገረ በአክሱም ስልጣኔ ዓለምን የናኘ ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ እንደነበራት የአደባባይ ሐቅ ነው። የአዱሊስ ወደብም አፍ አውጥቶ ይናገራል፤ ከመካከለኛው ዘመን እስከ ቅርቡ አሰብ ወደብ ኢትዮጵያና የባሕር በር የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ሆነው ቆይተዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሲቪልና የአካባቢ ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህር በለጠ ብርሃኑ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ከዓባይና የቀይ ባሕር ውሃዎች ጋር የተቆራኘ መሆኑን ያስታውሳሉ፡፡ የባሕር በር የሀገር ብሔራዊ ጥቅም አንጓ ሆኖ እያለ ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር የተገለለችበት መንገድ የሚያስቆጭና በሀገር ሉዓላዊነት ላይ የተፈፀመ በደል ነው ይላሉ። የኢትዮጵያ የወቅቱ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና መልክዓ-ምድራዊ ማስረጃዎች እንዳሉት ያብራራሉ። ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት ተመራጭ መንግሥትና ሕጋዊ የሕዝብ ውክልና ያልተሰጠው የሽፍታ ስብስብ ኤርትራን በማስገንጠል ኢትዮጵያን የባሕር በር አልባ አድርጓታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ይህንን ሕገ ወጥና በሀገር ላይ የተፈጸመ ክህደት ሲያብራሩ "ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበትን ውሳኔ ማን ወሰነው?" ሲሉ ይጠይቃሉ። ሲቀጥሉም "ካቢኔው ይሆናል ብለን የካቢኔውን ዶክመንት ብናነብ የለም፣ ካቢኔው አያውቅም። አይ የለም ምክር ቤት ይሆናል የወሰነው ብለን ብንወስድ ምክር ቤትም አልነበረም፣ ምክር ቤቱም አላወቀም። የለም የኢትዮጵያ ህዝብ በሪፈረንደም ወስኖ ይሆናል እንዳይባል አልወሰነም፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልወሰነውን፣ ተወካዮቹ ያላዩትን፣ ቢያንስ ቢያንስ አስፈጻሚው ካቢኔ ያላየውን ውሳኔ ማን ወሰነው? ማጣትን የሚያክል ነገር ያጣንበት መንገድ ሕጋዊነት ችግር እንዳለው የሚያሳየው፣ ተቋሞች አልገቡበትም" በማለት ውሳኔው ሕዝባዊና ተቋማዊ ውክልና ባልነበረው ስብስብ የተወሰነ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የሀገር ውስጥ ባንዳና ከውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በፈጠሩት ጥምረት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ኢ-ፍትሐዊ በደል ፈፅመዋል። ይህም ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት፣ በፍጥነት እያደገች ያለች ኢኮኖሚ ያላትና በቀጣናው የሰላምና የደኅንነት ዋና ተዋናይ የሆነችውን ኢትዮጵያ ያላቋረጠ የጂኦፖለቲካ ፈተና ውስጥ አስገብቷታል። በዚህ አውድ ውስጥ የቀረበው የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሌላ ሀገርን ግዛት ለመውሰድ ወይም ሉዓላዊነትን ለመጋፋት የቀረበ ጥያቄ አይደለም። ይልቁንም በሰላማዊ ውይይት፣ በጋራ ጥቅም፣ በቀጣናዊ ትብብር እና በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች መሠረት ሁሉንም ወገኖች የሚጠቅም ዘላቂ መፍትሔ ለማስገኘት የቀረበ የልማትና የሕልውና አጀንዳ ነው። የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ ከኢኮኖሚ ጥቅም በላይ የሀገር ዘላቂ ዕድገት፣ የቀጣናው ትስስር እና የብሔራዊ ሕልውና ጉዳይ ነው። ስለዚህም ጥያቄው ታሪካዊ እውነታን፣ ሕጋዊ መሠረትን፣ ጂኦግራፊያዊ እውነታን እና የጋራ ቀጣናዊ ጥቅምን በሚያጣምር መንገድ መታየት ያለበት ስትራቴጂካዊ ጉዳይ እንጂ የግጭት ወይም የመስፋፋት የፖለቲካ መገለጫ ተደርጎ የሚወሰድ አይደለም። 👉ባሕር፤ የታሪካችን አካል፣ የወደፊታችንም መሠረት የኢትዮጵያ ከባሕር ጋር ያላት ትስስር ከዛሬ የተጀመረ ሳይሆን ከሥልጣኔዋ መነሻ ጋር የተቆራኘ የአደባባይ ሐቅ ነው። የአክሱም ሥልጣኔ በአዱሊስ ወደብ በኩል ከሮማ፣ ከግብፅ፣ ከሕንድ፣ ከዓረቡ ዓለምና ከሩቅ ምሥራቅ ጋር የንግድና የሥልጣኔ ትስስር መፍጠሩ በታሪክ የተመዘገበ እውነታ ነው። በዚህ ወደብ አማካኝነት ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ቅመማ ቅመሞችና ሌሎች የንግድ ሸቀጦች ወደ ዓለም ገበያ ይደርሱ እንደነበርም ታሪክ ያስረዳል። በዚህ ረገድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኃይድሮ ፖለቲክስ ተመራማሪና ዓለም አቀፍ የውሃ ተደራዳሪ ያዕቆብ አርሳኖ (ዶ/ር) እንደሚገልጹት፣ የባሕር በር ጉዳይ በኢትዮጵያ ታሪክ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው የብሔራዊ ጥቅም ማጠንጠኛ ነው። ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ ከባሕር ጋር የነበራት ታሪካዊ ትስስር በተለያዩ የፖለቲካ ለውጦች ቢቋረጥም፣ በሕዝብ የልብ ማህደረ ውስጥ ያለው ስፍራ አልተሸረሸረም። ኢትዮጵያ በታሪኳ አሰብን፣ ምጽዋንና ሌሎች ወደቦችን ተጠቅማ ከቀጣናውና ከዓለም ጋር ሰፊ የንግድ ትስስር የፈጠረች ሀገር ናት። ስለዚህ የባሕር በር ጉዳይ አዲስ ፍላጎት ወይም አዲስ ፖለቲካዊ አጀንዳ ሳይሆን ከሀገሪቱ ታሪክ፣ ኢኮኖሚና ጂኦግራፊያዊ እውነታ ጋር የተቆራኘ ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው። ዛሬ ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በአቪዬሽን፣ በዲጂታል ኢኮኖሚና በኃይል ልማት ዘርፎች ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች ትገኛለች። ይሁን እንጂ ይህ የኢኮኖሚ መስፋፋት ውጤታማ የሎጂስቲክስ ሥርዓትና የተረጋጋ የባሕር በር ተደራሽነት ካልተደገፈ ሙሉ አቅሙን ማሳየት አይችልም። በዚህ ምክንያት የባሕር በር ጉዳይ የታሪክ ትውስታ ብቻ ሳይሆን፣ የዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ብልጽግና መሠረት ሆኗል። በመሆኑም የባሕር በር ጉዳይ የትናንትን ታሪክ ለመመለስ ብቻ ሳይሆን፣ የነገዋን ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለማጠናከር፣ የንግድ ወጪዎችን ለመቀነስ፣ የቀጣናዊ ትብብርን ለማስፋትና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያገለግል ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው። ከዚህ አንጻር በቀይ ባሕር አካባቢ በቅርብ ርቀት የምትገኘው ኢትዮጵያ ከባሕር ተደራሽነት ውጭ መሆኗ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገትና በቀጣናዊ ተወዳዳሪነት ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ በተረጋጋ የውይይትና የትብብር መንገዶች መፍትሔ የሚሻ ስትራቴጂክ ጉዳይ መሆኑን ያሳያል። 👉የባሕር በር፤ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ የልማትና የሕልውና ጥያቄ በ21ኛው ክፍለ ዘመን የአንድ ሀገር ጥንካሬ በወታደራዊ ኃይል ብቻ ሳይሆን፣ በኢኮኖሚ ተወዳዳሪነት፣ በንግድ ትስስር፣ በሎጂስቲክስ ቅልጥፍናና ዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነት ይለካል። በዚህ መለኪያ የባሕር በር ለኢትዮጵያ የቅንጦት ሳይሆን የልማት መሠረታዊ መስፈርት ሆኖ ይታያል። በዚህ አውድ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ታሪካዊ እውነታን፣ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥንና ዓለም አቀፍ የሕግ መርሆዎችን ያጣመረ የልማት ጉዳይ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ። ኢትዮጵያ ለዚህ ጥያቄ መፍትሔ ለማግኘት የምታደርገው ጥረትም በሰላማዊ ውይይት፣ በዲፕሎማሲ፣ በጋራ ጥቅምና በቀጣናዊ ትብብር ላይ የተመሠረተ ነው። ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት፣ በአፍሪካ በፍጥነት እያደገች ያለች፣ በአቪዬሽን፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በኃይልና በዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየገነባች ያለች ኢትዮጵያ፣ ይህን የልማት እመርታ በተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ሥርዓትና በተረጋጋ የባሕር በር ተደራሽነት ካልደገፈች ሙሉ አቅሟን ማሳካት አትችልም። በዚህ ምክንያት የባሕር በር ጉዳይ የአንድ ወደብ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን፣ የንግድ ተወዳዳሪነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ብልፅግና ጉዳይ ነው። እንደዚሁም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ደጋግመው እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ ጥያቄ የጦርነት ወይም የመስፋፋት ሳይሆን፣ በሰላማዊ ውይይት፣ በጋራ ጥቅምና በቀጣናዊ ትብብር መሠረት መፍትሔ የሚፈልግ የልማትና የሕልውና ጉዳይ ነው። 👉የኢኮኖሚ እመርታና የባሕር በር ትስስር በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ኢትዮጵያ በብዝኅ ኢኮኖሚ ሥርዓት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና ዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፎች መሠረታዊ ለውጦችን አስመዝግባለች። የግብርና ምርት ጨምሯል፣ የኢንዱስትሪ ማምረት አቅም ጎልብቷል፣ የማዕድን ሀብቶች ወደ ውጭ ገበያ እየቀረቡ ሲሆን፣ የቱሪዝምና የዲጂታል ኢኮኖሚ መስፋፋትም አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ከፍቷል። ይሁን እንጂ ይህ እመርታ ተወዳዳሪና ዘላቂ ሊሆን የሚችለው ከተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ሥርዓትና ከአስተማማኝ የባሕር በር ተደራሽነት ጋር ሲተሳሰር ነው። የግብርና ምርቶች፣ የኢንዱስትሪ ውጤቶች፣ የማዕድን ሀብቶችና ሌሎች ወደ ዓለም ገበያ በፍጥነትና በወጪ ቆጣቢነት እንዲደርሱ የባሕር በር ወሳኝ ሚና ይጫወታል። የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) እንደሚገልጹት፣ የኢትዮጵያና የቀይ ባሕር ትስስር ከሀገረ መንግሥቷ ታሪክ ጋር የተቆራኘ ሲሆን፣ የባሕር በር ጉዳይም የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የብሔራዊ ጥቅም ቁልፍ አጀንዳ ነው። በተለይም ኢትዮጵያ በየዓመቱ ለወደብና ለሎጂስቲክስ አገልግሎት ብቻ ከ1.5 እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓ፣ የባሕር በር ጉዳዩ ከኢኮኖሚ ጋር ያለውን ቀጥተኛ ትስስር ያሳያል። የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎችም እንደሚጠቁሙት፣ አስተማማኝ የባሕር በርና አማራጭ የወደብ አገልግሎት ለኢትዮጵያ ቅንጦት ሳይሆን የፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገቷን ለማስቀጠል የሚያስፈልግ መሠረታዊ ፍላጎት ነው። ስለዚህ የባሕር በር ጉዳይ የአንድ ዘርፍ ፍላጎት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን፣ የንግድ መስፋፋትንና የዘላቂ ብልጽግና ጉዞን የሚወስን ስትራቴጂካዊ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ነው። 👉ከታሪካዊ መብት ወደ የጋራ ብልፅግና፤ ምላሽ የሚሻው የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ!! የኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ የትናንትን ታሪክ ለማስታወስ ብቻ የቀረበ አይደለም፤ የነገውን የቀጣናው ኢኮኖሚ፣ የንግድ ትስስርና የጋራ ብልፅግና የሚወስን ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ሀገራት ፉክክርን ሳይሆን ትብብርን ከመረጡ፣ ወደቦች የአንድ ሀገር ብቻ ሳይሆኑ የቀጣናውን የጋራ ዕድገት ማስፈንጠሪያ መድረኮች ይሆናሉ። በዚህ እሳቤም የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለቀይ ባሕር ቀጣና፣ ለአፍሪካ ቀንድ እና ለቀጣናዊ ሰላምና ኢኮኖሚያዊ ትስስር አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት የሚያስችል ዕድል ነው። የምጣኔ ሀብት ምሁር ጀማል መሐመድ (ዶ/ር) እንደሚገልጹትም፣ የኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት አስተማማኝ የባሕር በር ተደራሽነትን ይሻል፤ ይህ አለመኖሩ ግን የንግድ ተወዳዳሪነትን በመገደብ በሀገሪቱ ኢኮኖሚና በዜጎች ተጠቃሚነት ላይ ቀጥተኛ ጫና ያሳድራል። ስለዚህ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የግዛት መስፋፋት ሳይሆን፣ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ሀገር ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገቷን ለማረጋገጥ፣ የንግድ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግና የቀጣናዊ የጋራ ብልፅግናን ለማጠናከር የሚቀርብ የልማትና የሕልውና ጥያቄ ነው። 👉የቀይ ባሕር ጂኦፖለቲካ፤ የዓለም ትኩረት ለምን በቀጣናው ላይ ነው? የቀይ ባሕር ከውሃ አካልነቱ ባሻገር የዓለም ኢኮኖሚና የጂኦፖለቲካ ወሳኝ ማዕከል ነው። ከሕንድ ውቅያኖስ እስከ ሜዲትራኒያን የሚዘረጋው ይህ የባሕር መስመር የእስያን፣ የአፍሪካንና የአውሮፓን ኢኮኖሚዎች የሚያገናኝ ዋነኛ የዓለም የንግድ መተላለፊያ ነው። በዚህ ቀጣና የሚያልፉ መርከቦች ሸቀጦችን ብቻ ሳይሆን የኃይል አቅርቦትን፣ የምግብ ዋስትናንና የዓለም ኢኮኖሚ ቀጣይነትንም ይሸከማሉ። ስለዚህም የቀይ ባሕር ደህንነት የአንድ ቀጣና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የዓለም አቀፍ ጉዳይ ሆኗል። በቀጣናው የሚፈጠር ማንኛውም መስተጓጎል የነዳጅና የምግብ ዋጋ፣ የመጓጓዣ ወጪ እንዲሁም የዓለም የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ ያሳድራል፤ ስለዚህ ዓለም የቀይ ባሕርን በልዩ ትኩረት ትከታተላለች። 👉ኢትዮጵያ፤ የቀጣናው ተፈጥሯዊ ማዕከል ኢትዮጵያ ለሦስት አስርት ዓመታት ከቀይ ባሕር ዳርቻ ተገልላ ብትቆይም፣ የቀጣናው ትልቁ ኢኮኖሚ፣ ገበያና የሰው ኃይል ማዕከል ሆና ቀጥላለች። ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ፣ በፍጥነት እያደገ ያለ ኢኮኖሚ፣ ጠንካራ የአየር መጓጓዣ ትስስር፣ ትልልቅ የኃይል ፕሮጀክቶችና እየሰፋ ያለ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ያላት ሀገር፣ በቀይ ባሕር ጂኦ-ኢኮኖሚ ውስጥ ማዕከላዊ ሚና እንዳይኖራት ማሰብ አይቻልም። በመሆኑም የኢትዮጵያ ፍላጎት ወደ ባሕር መድረስ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጣናው ዘላቂ የኢኮኖሚ ትስስርና የጋራ ብልፅግና የሚያገለግል አስተማማኝና ተመጣጣኝ የባሕር በር ተደራሽነት ማረጋገጥ ነው። ይህም ለጎረቤት ሀገራት የንግድ፣ የኢንቨስትመንት፣ የሥራ ዕድልና የመሠረተ ልማት መስፋፋትን በማፋጠን የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያጠናክር እድል ይፈጥራል። 👉ከታሪክ ወደ የጋራ ጥቅም የቀይ ባሕር ቀጣና በታሪክ ዘመናት የሥልጣኔ፣ የንግድና የባህል መገናኛ ሆኖ ቆይቷል። ከአክሱም ጀምሮ እስከ ዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ድረስ የባሕር በር ከሀገሪቱ ኢኮኖሚና ታሪክ ጋር የተሳሰረ ተፈጥሯዊ አካል ነው። ይህን ታሪክ ማስታወስም ያለፉ ግጭቶችን ለመቀስቀስ ሳይሆን፣ የዛሬውን ጉዳይ በትክክለኛ ታሪካዊ እና ስትራቴጂያዊ አውድ ለመረዳት ነው። በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ከታሪካዊ መብት ባሻገር፣ ከኢኮኖሚ ዕድገት፣ ከሕዝብ ብዛት፣ ከቀጣናዊ ትስስርና ከጋራ ብልፅግና አንፃር ሊታይ ይገባል። ዘላቂ መፍትሔም በዓለም አቀፍ ሕግ፣ በጋራ ጥቅም፣ በኢኮኖሚ ትብብርና በተቋማዊ ውይይት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፣ ለኢትዮጵያም ሆነ ለመላው የቀይ ባሕር ቀጣና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያጎለብት ሊሆን ይገባል። 👉የወደፊቷ ኢትዮጵያ፤ ከብሉ ኢኮኖሚ ጋር የተሳሰረ ርዕይ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ፣ ከዚያም ወደ እሴት ጨማሪ ምርትና ዲጂታል ኢኮኖሚ እየተሸጋገረ ነው። ይህ ሽግግር ዘላቂ እንዲሆን ግን ውጤታማ የሎጂስቲክስ ሥርዓትና አስተማማኝ የባሕር በር ተደራሽነት ወሳኝ ነው። በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ የባሕር በር አጀንዳ የፖለቲካ ክርክር ሳይሆን የትውልድ የልማት ራዕይ ነው። በሕግ፣ በዲፕሎማሲና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ኢትዮጵያን ከዓለም ገበያ በተሻለ ሁኔታ ያገናኛል፤ ለቀጣናውም መረጋጋትና የጋራ ብልፅግና መሠረት ይሆናል። ስለዚህ የባሕር በር ጉዳይ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ዕድገትና የብሉ ኢኮኖሚ የወደፊት ራዕይ አካል ነው። 👉መደምደሚያ፡ የባሕር በር ጉዳይ፤ የግጭት ሳይሆን የጋራ ብልፅግና መንገድ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ያለፈውን ታሪክ ለመመለስ ብቻ የቀረበ ጥያቄ ሳይሆን፣ የወደፊቱን የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ብልፅግና የሚወስን ስትራቴጂያዊ አጀንዳ ነው። የባሕር በር ተደራሽነት የሌላ ሀገር ጥቅምን በመጉዳት ሳይሆን፣ በጋራ ጥቅም፣ በኢኮኖሚ ትብብርና በቀጣናዊ ልማት ላይ የተመሠረተ የዕድገት መንገድ ነው። በ21ኛው ክፍለ ዘመን የሀገራት ብልፅግና በመገፋፋት ሳይሆን በመተባበርና በጋራ ዕድገት ይገነባል። ስለዚህ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ለቀጣናው የኢኮኖሚ ትስስር፣ ለንግድ መስፋፋትና ለዘላቂ ሰላም አዲስ ዕድል የሚከፍት ነው። ከአክሱም ሥልጣኔ ጀምሮ ከቀይ ባሕር ጋር የቆየው ታሪካዊ ትስስር ከዘመኑ የሕዝብ ብዛት፣ ከኢኮኖሚ ዕድገትና ከቀጣናዊ ሚና ጋር ተያይዞ አዲስ ስትራቴጂያዊ አስፈላጊነት አግኝቷል። ስለሆነም አስተማማኝ የባሕር በር ተደራሽነት ማረጋገጥ የዛሬው ትውልድ የልማት ራዕይና የጋራ ኃላፊነት ነው። ይህም በጽኑ ሀገራዊ አንድነት፣ በበሰለ ዲፕሎማሲ፣ በውይይትና በጋራ ጥቅም መርህ ሊመራ ይገባል። በመጨረሻም የባሕር በር የትናንት ትዝታ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ የነገ ብልፅግና፣ የቀጣናው የጋራ ልማትና የአፍሪካ ተስፋ መንገድ ነው። የባሕር በር የኢትዮጵያ የነገ ብልፅግና መንገድ እንጂ የትናንት ትዝታ ብቻ አይደለም!!
ምግቤን ከደጄ፤ የከተማ ግብርና አዲሱ የምግብ ዋስትና መሰረት
Jul 25, 2026 229
በመቅደስ ወልዴ መግቢያ፡- ዛሬ ዓለም በፈጣን የከተሜነት ሽግግር ውስጥ ትገኛለች። በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ከገጠር ወደ ከተማ በመፍለስ፣ ከተሞችን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንትና የኑሮ ማዕከላት እያደረጓቸው ነው። ይህ ሽግግር አዳዲስ የልማት ዕድሎችን ቢፈጥርም፣ ከምግብ አቅርቦት እስከ የኑሮ ውድነት፣ ከአካባቢ ጥበቃ እስከ የሥራ ፈጠራ ድረስ ያሉ አዳዲስ ፈተናዎችንም አስከትሏል። በተለይም በታዳጊ ሀገራት የከተሞች መስፋፋት የምግብ ዋስትናን ከልማት ፖሊሲዎች ማዕከል ላይ አስቀምጦታል። በ2050 ከዓለም ሕዝብ ሁለት ሦስተኛው በከተሞች እንደሚኖር የሚጠበቀው እውነታ፣ ከተሞች ምግባቸውን ለማረጋገጥ አዳዲስና ዘላቂ መፍትሔዎችን እንዲፈልጉ አስገድዷቸዋል። ኢትዮጵያም ከዚህ ዓለም አቀፋዊ ሽግግር ውጭ አይደለችም። የከተማ ነዋሪዎች ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ፣ የምግብ አቅርቦት፣ የገበያ መረጋጋትና የኑሮ ውድነት አዳዲስ የፖሊሲ ጉዳዮች ሆነው ተነስተዋል። በዚህ ዐውድ ውስጥ የከተማ ግብርና ባዶ ቦታን ወደ ምርት፣ ቆሻሻን ወደ ማዳበሪያ፣ ሸማቹን ወደ አምራች የሚቀይር ዘመናዊና ዘላቂ የልማት መንገድ ሆኖ እየጎለበተ ነው። የከተማ ግብርና፤ ምንነቱና ጠቀሜታው የከተማ ግብርና በከተማ ውስጥ በሚገኙ አነስተኛ ቦታዎች፣ በመኖሪያ ግቢዎች፣ በሕንፃ ጣሪያዎችና በበረንዳ ስፍራዎች ላይ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ቀላል የምርት ዘዴዎችን በመጠቀም አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ እንስሳት፣ ዓሳና ሌሎች የግብርና ውጤቶችን የማምረት ሥርዓት ነው። ቀደም ሲል ግብርና የገጠር ብቻ ተደርጎ ይታሰብ የነበረው አመለካከት ዛሬ በእጅጉ ተለውጧል። በከተሞች የሚገኙ ጠባብ ስፍራዎች እንኳን ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የልማት መስኮች ሆነዋል። በቤት ዙሪያ ይደረግ የነበረው ቀላል የጓሮ አትክልት ልማትም ዛሬ ለሺዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ፣ ገበያን የሚያረጋጋና የሀገር ኢኮኖሚን የሚደግፍ ዘርፍ ሆኗል። ከተሞችን ውብና አረንጓዴ ከማድረጉ ባሻገር፣ ነዋሪዎች በራሳቸው ምርት የምግብ ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ፣ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙና ለአካባቢ ጥበቃ ተጨባጭ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ አስችሏቸዋል። እንዲሁም የዶሮ እርባታ፣ የንብ ማነብና ሌሎች አነስተኛ የግብርና ሥራዎች የቤተሰብን ምግብ ከማሟላት ባለፈ ገበያውን በማረጋጋት ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። የከተማ ግብርና ለምን አስፈለገ? የግብርና ልማት ዛሬ በገጠር አርሶ አደሮች ጥረት ብቻ የሚገደብ አይደለም። የከተሞችን እምቅ ሀብት በመጠቀምና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በማቀናጀት የኑሮ ውድነትን መቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና አረንጓዴ ኢኮኖሚን መገንባት የሚቻልበት ውጤታማ መንገድ መሆኑ በተግባር ተረጋግጧል። ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ተሞክሮዎችም የከተማ ግብርና የከተሞችን ገበያ በማረጋጋት፣ ለወጣቶችና ለሴቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የከተማ ቆሻሻን ወደ ተፈጥሯዊ ማዳበሪያ በመቀየርና የከተሞችን አረንጓዴነት በማጎልበት ያለውን ጉልህ አስተዋጽኦ በተግባር አሳይተዋል። የከተማ ግብርና፤ ከጓሮ ልማት ወደ ሀገራዊ የልማት ስትራቴጂ ቀደም ሲል በቤት ጓሮ የሚከናወን ቀላል የአትክልት ልማት ተደርጎ ይታይ የነበረው የከተማ ግብርና፣ ዛሬ የምግብ ዋስትናን፣ የገበያ መረጋጋትን፣ የሥራ ፈጠራንና የአረንጓዴ ኢኮኖሚን የሚያጠናክር ሀገራዊ የልማት ስትራቴጂ ሆኖ ተቀይሯል። በአነስተኛ ቦታዎች፣ በቤት ግቢዎች፣ በሕንፃ ጣሪያዎችና በባዶ መሬቶች ላይ የአትክልት፣ የፍራፍሬ፣ የዶሮ እርባታ፣ የወተት ሀብት፣ የንብ እርባታና ሌሎች የግብርና ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ። "ምግቤን ከደጄ" የሚለው ሀገራዊ ንቅናቄም የከተማ ነዋሪዎች በራሳቸው ምርት የምግብ ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ አዲስ ዕድል ፈጥሯል። የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ እስከ የገበያ መረጋጋት የከተማ ግብርና ከሚያስገኛቸው ትልልቅ ጥቅሞች መካከል ዋነኛው የምግብ ምርትን ለተጠቃሚው በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ወጪና በተሻለ ጥራት ማድረስ መቻሉ ነው። በከተማ ውስጥ የሚመረቱ አትክልቶች፣ ፍራፍሬዎች፣ እንቁላልና ወተት ረጅም ርቀት ሳይጓዙ በቀጥታ ለገበያ ስለሚቀርቡ ትኩስነታቸውን ይጠብቃሉ፤ የመጓጓዣ ወጪንም በእጅጉ ይቀንሳሉ። በሌላ በኩል ቤተሰቦች በጓሯቸው የሚያመርቱት ምርት የዕለት ተዕለት የምግብ ወጪያቸውን በመቀነስ የምግብ ዋስትናቸውን ያጠናክራል። ከቤተሰብ ፍጆታ በላይ የሚተርፈው ምርት ደግሞ ወደ ገበያ በመግባት የምግብ አቅርቦትን ያሳድጋል፤ በዚህም የዋጋ ንረትን በመቀነስ የገበያ መረጋጋትን ለማስፈን የጎላ አስተዋፅኦ ያደርጋል። የአረንጓዴ ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ የከተማ ግብርና የምግብ ምርትን ከማሳደግ ባለፈ፣ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር የከተማ ኢኮኖሚን የሚያነቃቃና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ መሠረትን የሚያጠናክር ዘርፍ ሆኗል። በአዲስ አበባን ጨምሮ በበርካታ የኢትዮጵያ ከተሞች በአትክልት፣ በፍራፍሬ፣ በዶሮ እርባታ፣ በወተት ሀብትና በንብ ማነብ የተሰማሩ በርካታ ወጣቶችና ሴቶች ቋሚ የገቢ ምንጭ እያገኙ ይገኛሉ። ይህም የከተማ ግብርና የቤተሰብ የምግብ ፍላጎትን ከማሟላት ባሻገር የሥራ አጥነትን ለመቀነስና የከተማ ኢኮኖሚን ለማጠናከር እያበረከተ ያለውን ጉልህ አስተዋፅኦ ያሳያል። አካባቢን ከመጠበቅ እስከ የከተሞችን ውበት የከተማ ግብርና የሥነ-ምህዳር ጠቀሜታውም ከፍተኛ ነው። ከቤት የሚወጡ ኦርጋኒክ ቆሻሻዎችን ወደ ተፈጥሯዊ ማዳበሪያ በመቀየር የአፈር ለምነትን ያሻሽላል፤ በተመሳሳይ ጊዜም የከተማ ጽዳትን ያጠናክራል። ከዚህ በተጨማሪ የአረንጓዴ ስፍራዎች መስፋፋት የከተሞችን የሙቀት መጠን በመቀነስ፣ የአየር ጥራትን በማሻሻልና ለነዋሪዎች ጤናማና ምቹ የኑሮ አካባቢ በመፍጠር ለከተማ ዘላቂነት የጎላ አስተዋፅኦ ያደርጋል። ማጠቃለያ የከተማ ግብርና የኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት የልማት አቅጣጫ መሆኑን በተግባር አረጋግጧል። የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ጀምሮ የኑሮ ውድነትን መቀነስ፣ የሥራ ፈጠራን ማስፋፋት፣ የከተሞችን ውበት ማጎልበትና የአረንጓዴ ኢኮኖሚን መገንባት ድረስ ያለው ሚና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎላ ነው። ስለሆነም ለከተማ ግብርና የሚስማሙ ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋት፣ ለወጣቶችና ለሴቶች የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍን ማጠናከር፣ የገበያ ትስስርን ማሻሻልና በከተማ ፕላን ውስጥ ለግብርና ተስማሚ ቦታዎችን በቋሚነት መመደብ ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው። ከተሞች የምግብ ፍጆታቸውን በራሳቸው የማምረት አቅም እያዳበሩ ሲሄዱ፤ የኢትዮጵያ ዘላቂ የምግብ ዋስትና፣ ጠንካራ አረንጓዴ ኢኮኖሚና ተወዳዳሪ የከተማ ልማት ስኬታማ ትልም ይበልጥ ይፋጠናል። ከደጃችን የሚጀምረው ምርት፤ ለሀገር ዕድገት የሚሆን ትልቅ አቅም ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ፤ ከሥነ-ምኅዳር ዘብ እስከ ዓለም የልማት ተምሳሌት
Jul 23, 2026 448
በመጽሔት አንለይ በወሳኝ ሀገራዊ የልማት ውይይቶች ላይ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸው፣ በዚህም በርካታ ሚሊየን ሄክታር መሬት መታደሱ እንዲሁም የተመዘገበ የደን ሽፋን በአበይት ጉዳይነት ይነሳሉ። ኢትዮጵያ እየተገበረችው ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የአርሶ አደሩ ምርታማነት ማደግ፣ የወጣቱ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን፣ የእናቶች የኑሮ መሻሻልና የተፈጥሮ ሃብት መጠበቅ መቻሉ እንዲሁም የአየር ንብረት መዛባትን ማስተካከልና የደን ሽፋንን ማሳደጉ ለመርሃ ግብሩ ውጤታማነት በአብነትነት ይጠቀሳሉ። በዚህ አተያይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተራ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ባሻገር በአካባቢ ጥበቃ፣ በግብርና፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ልማት ዘርፎች መዋቅራዊ ለውጥ በማምጣት አንጸባራቂ ውጤት እያሰገኘ ነው። የዓለም አየር ንብረት ጉዳይ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ባለበት ወቅት፣ አፍሪካ የችግሩ ተጠቂ ብቻ ሳትሆን ለመፍትሄውም የራሷን ልምድና አቅም ማበርከት እንደምትችል እያሳየች ይገኛል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሀገራዊ ንቅናቄም ለአፍሪካ የአካባቢ ጥበቃ ጥረት አዲስ የተግባር ልምድ እየሆነ መጥቷል። የአረንጓዴ ዐሻራው ልዩነት በተተከሉ ችግኞች ቁጥር ብቻ አይለካም። በተራቆቱ መሬቶች ላይ የተመለሰው ሕይወት፣ በገጠር የተፈጠሩ የኢኮኖሚ ዕድሎች፣ የተጠበቁ የውሃ ሀብቶችና ለወደፊት ትውልድ የተገነባው የአካባቢ መሠረት ዋናው ውጤቱ ነው። አረንጓዴ ዐሻራ፤ ከርዕይ ወደ ተግባር!! የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሀገራዊ ለውጥ ማግስት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በሕዝባዊ ተሳትፎ የተጀመረ ሲሆን፤ እስካሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ከዚህ በፊት የነበረው የተፈጥሮ ሃብት መራቆት በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ብቻ ሳይሆን በዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይም ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ ነበር። የአፈር መሸርሸር፣ የደን መጥፋትና የድርቅ ተጋላጭነቶችም የገጠር ሥነ-ምኅዳራዊ ሕይወትን ሲፈታተኑ ቆይተዋል። ይህን ምላሽ ለመስጠትም የአረንጓዴ ዐሻራ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማልማትና የደን ሽፋንን ከነበረበት 17 ነጥብ 2 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በማሳደግ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። የአረንጓዴ አሻራ የኢኮኖሚ ዐሻራ፡- የአረንጓዴ ዐሻራ ትርጉም በአካባቢ ጥበቃ ብቻ አይወሰንም። በኢኮኖሚውም ውስጥ አዲስ የልማት መንገድ እየፈጠረ ይገኛል። በጥምር ግብርና (Agroforestry) አማካኝነት ቡና፣ ፍራፍሬና ሌሎች የኢኮኖሚ ዋጋ ያላቸው ምርቶች ከደን ልማት ጋር እንዲሰናሰሉ አድርጓል። ይህም የገቢ ምንጭን ከማስፋት ባሻገር የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ አስተዋፅዖ አድርጓል። በተለይ የቡና ዘርፍ ከሚሊዮን ወደ ቢሊዮን ዶላር ደረጃ መሻገሩ የዚህ ጥምረት ውጤት አንዱ ማሳያ ነው። የአቮካዶ ምርት ለወጪ ንግድ የፈጠረው ዕድልም አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ ውጤታማነት አብነት ሆኗል። በሌሎች የፍራፍሬ ምርቶች ላይ የመጣው ዕድገት ኢትዮጵያን በዓለም ገበያ የተሻለ ተወዳዳሪ የምትሆንበትን ዕድል ፈጥሯል። ከአፈር ጥበቃ እስከ ምግብ ዋስትና፡- የአረንጓዴ ዐሻራ በአፈር ጤናማነት ላይ ያመጣው ለውጥ የግብርና ምርታማነትን ከፍ አድርጓል። የአፈር ኦርጋኒክ ካርቦን መጨመር፣ የውሃ ማቆየት አቅም መሻሻልና የተፋሰስ ልማት በኢትዮጵያ የመስኖ ልማትና የምግብ ምርት ዕድገት መሠረት ጥለዋል። የስንዴ ምርታማነት ዕድገት እና የቤተሰብ ብልፅግናን የሚያረጋግጥ ስኬታማ ጉዞም የአረንጓዴ ዐሻራ ተጠቃሽ ውጤቶች ናቸው። የተፈጥሮ ጋሻነት፡- ኢትዮጵያ ለድርቅ፣ ለጎርፍና ለመሬት መንሸራተት ተጋላጭ ከሆኑ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት። ዛፎችና ስሮቻቸው አፈርን በመያዝ መሸርሸርን ይቀንሳሉ፤ የውሃ ሃብቶችን ጠብቆ በማቆየትና በማሻሻል የድርቅ ተጋላጭነትን የመቋቋም አቅም እየገነባ ነው። በተለይም በርካታ የኃይል ማመንጫ ግድቦችንና የውሃ ሃብቶችን ከደለል አደጋ ለመጠበቅ የደን ልማት ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ እሙን ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም የተፈጥሮ አደጋዎችን በመቀልበስ የተፈጥሮ ጋሻነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። የትውልድ ሐውልትና የልማት ውርስ የሆነው አረንጓዴ ዐሻራ!! የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የመንግሥትና የሕዝብ የጋራ ተሳትፎ ውጤት መሆኑን የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ በአንድ ወቅት ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻም፣ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ዘመቻ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ተሳትፈውበታል። ይህም ኢትዮጵያዊያን የጋራ ታሪክ በመፃፍ በልማት መስክ አስደናቂ የትብብር መንፈስ እንዲገነቡ አስችሏል። የመርሃ ግብሩ ብሔራዊ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አረንጓዴ ዐሻራ የደን ውድመትን በመከላከል የተፈጥሮ ሃብትን ለመጠበቅ፣ የድርቅና የበረሃማነት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እያስገኘ ነው። የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተፅዕኖ መቋቋም አዲስ የዲፕሎማሲ ሚና!! በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረክ የአፍሪካ ዋና ጥያቄ የአየር ንብረት ፍትሐዊነት ነው። አህጉሪቱ በአነስተኛ የካርቦን ልቀት ላይ ብትገኝም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ከባድ ጫናን እየተጋፈጠች ይገኛል። በዚህ አውድ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራን እንደ ሀገራዊ ፕሮጀክት በመውሰድ ለአፍሪካ ሀገራት ጭምር የሚጋራ ተሞክሮ ፈጥራለች። የአፍሪካ አህጉራዊ የአየር ንብረት ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄዱም ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ ያላትን ተሳትፎና አመራር ያሳየ ክስተት ነው። ይህ ጉባኤ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የአየር ንብረት ውይይት ማዕከል እንድትሆን ከማገዙም በላይ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮችን ለማስተናገድ ያላትን አቅም በተግባር አሳይቷል። ማጠቃለያ፡- የተተከለ ችግኝ፣ የተገነባ ተስፋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ ''ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት፤ በዚህ ዓመት ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምቷል። በዚሁ ወቅትም ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን ወደ 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በፅናት እየገሰገስን እንገኛለን ብለዋል፡፡ ዘንድሮም የተያዘውን የስምንት ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ስራ ላይ በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ መትከል ብቻ አይደለም። የኢትዮጵያ የወደፊት የዕድገትና ብልፅግና ማሳኪያ የልማት ትልም እንጂ። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም ከአንድ ችግኝ ጀምሮ እስከ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረክ የደረሰ የሀገር ተሞክሮ ነው። የተተከሉት ችግኞች ዛሬ የአካባቢ ጥበቃ ዘብ ሲሆኑ፣ ነገ ደግሞ የኢኮኖሚ ዕድል፣ የምግብ ዋስትና፣ የኃይል ዘላቂነትና የትውልድ ተስፋ ይሆናሉ። የተተከለው ችግኝ ነገ የሚሆነው ዛፍ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬ፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ጋሻና ለመጪው ትውልድ የሚተላለፍ ሕያው ቅርስ ነው። አረንጓዴ ዐሻራ ዛሬ የሚተከል ተስፋ፣ ነገ የሚሰበሰብ ብልፅግና ነው፤ ተስፋን እንትከል!!!
የሌማት ትሩፋት፡ የኢትዮጵያ ግብርና በአዲስ ምዕራፍ
Jul 22, 2026 388
በሳባ ስለሺ መግቢያ ኢትዮጵያ ለዘመናት የነበራትን የግብርና እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ የምግብ ዋስትና ለመቀየር ተግዳሮት ሆኖባት የቆየ ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግስት በተጀመረው ዘርፈ-ብዙ የሪፎርም ጉዞ የዘርፉ ታሪክ በተጨባጭ እየተቀየረ ነው። የዚህ ለውጥ አብይ ማሳያ የሆነውና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ ይፋ የሆነው "የሌማት ትሩፋት" መርሃ ግብር አንዱ ነው። ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ የሀገሪቱን የግብርና እና የእንስሳት ሀብት ልማት ጉዞ በአዲስ ምዕራፍ የቃኘ ነው። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ሲሆን፣ በዋናነት በእንስሳት ሀብት እና ተያያዥ ዘርፎች ላይ ያተኩራል።በእንስሳት ሀብት ልማት ረገድ የወተት ላሞችን፣ የዶሮ (ሥጋ እና እንቁላል)፣ የንብ ማነብ (ማር) እና የዓሣ እርባታን በስፋት የሚያካትት ነው።የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ ኢትዮጵያን ከምግብ ሸማችነት ወደ አምራችነት በማሸጋገር የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ነው። በተለይም በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ የኑሮ ውድነትን በማቃለል፣ የአርሶና አርብቶ አደሩን ገቢ በማሳደግ እንዲሁም ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት የምግብ ሉዓላዊነትን እውን ለማድረግ ያለመ ነው። የሌማት ትሩፋት ለምን አስፈለገ? ፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር፣ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የተፈጥሮ ሀብትና የሰው ኃይል በመጠቀም፣ ለዘመናት የዘለቀውን የምግብና ሥነ-ምግብ ዋስትና ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተነደፈ ነው። መንግስት ለዚህ መርሃ ግብር ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት የሚገኘውም፣ ሀገሪቱ ያላትን ከፍተኛ የእንስሳት ሀብት በቴክኖሎጂ በመደገፍ ወደ ተጨባጭ እሴትና የሀገር ውስጥ ተጠቃሚነት ለመቀየር እንዲሁም የዘርፉን ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ነው። ባለፉት አራት ዓመታት ምን ተከናወነ?፡- ባለፉት አራት ዓመታት በተተገበረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የወተት፣ የእንቁላል፣ የሥጋ፣ የዓሣ እና የማር ምርቶችን ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ ተከናውኗል። ለዚህ ስኬት በቂና ጥራት ያለው የእንስሳት ተዋጽኦ ለማቅረብ የሚያስችሉ ሰፊ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻልና የማዳቀል ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን፤ የአዳቃይ ቴክኒሻኖችን አቅም መገንባት፣ የፈሳሽ ናይትሮጂን አቅርቦትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለዘርፉ ተዋናዮች ማስተላለፍ ተችሏል። እንዲሁም የእንስሳት መኖ አቅርቦትንና ተደራሽነትን በማስፋፋት፣ የእንስሳት እርባታ ደህንነታቸውን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወን በማድረግ እና አስፈላጊውን መሰረተ ልማት በማሟላት ረገድ ላለፉት አራት ዓመታት ቅድሚያ ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል። በመስኩ ምን ተጨባጭ ውጤት ተገኘ ?፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የሀገሪቱን የምግብና ስነ-ምግብ ደህንነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በዜጎች ዘንድ የቆየውን አመለካከት በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ለውጥ አስመዝግቧል። በተለይም በገጠሪቱ የሀገሪቱ ክፍል ብቻ ተወስኖ የነበረውን የግብርና እንቅስቃሴ ወደ ከተሞች በማስፋት፣ ህጻናት፣ እናቶች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ከእንስሳት ተዋጽኦ ማግኘት የሚገባቸውን አስፈላጊ ንጥረ ነገሮች እንዲያገኙ አስችሏል። ይህ ተነሳሽነት የከተማ ግብርናን በማስተዋወቅ ዜጎች በቤታቸው እንስሳትን በማርባት ከራስ ፍጆታ ባለፈ ምርቶቻቸውን ለገበያ በማቅረብ የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። በመሆኑም፣ ባለፉት ዓመታት በመስኩ የተመዘገቡት ስኬቶች እንደሚያሳዩት፣ መርሃ ግብሩ ዜጎች በተቋማት ተቀጥረው ከመስራት ይልቅ በዘርፉ ተሰማርተው የራሳቸው ስራ ኖሯቸው ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ አድርጓል። ይህ የመንግስት ያላሰለሰ ጥረት፣ የዜጎችን የስነ-ምግብ ፍላጎት ከማሟላት አልፎ፣ ጤናማ እና ሁለንተናዊ ብቃት ያለው ትውልድ በመገንባት ሂደት ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በአሀዛዊ መረጃ የተደገፉ የዘርፉ ስኬቶች ፡- የግብርና ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው አኃዛዊ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በተጀመረ በአራት ዓመታት (2014 ዓ.ም -2018 ዓ.ም) ውስጥ በእንስሳት ምርታማነት አስደናቂ ለውጥ ተመዝግቧል። በወተት ምርት፦ መርሃ ግብሩ ሲጀመር የነበረው 7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ሊትር የማምረት አቅም፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 15 ነጥብ 7 ቢሊዮን ሊትር አድጓል። በእንቁላል ምርት፦ ከነበረበት 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን በከፍተኛ ሁኔታ በማደግ፣ ወደ 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ከፍ ብሏል። በዶሮ ሥጋ ምርት፦ በ2014 ዓ.ም 90 ሺህ ቶን የነበረው የማምረት አቅም፣ በ2018 ዓ.ም ወደ 253 ሺህ ቶን ከፍ ብሏል። በማር ምርት፦ በ2014 ዓ.ም 146 ነጥብ 7 ሺህ ቶን የነበረው የማምረት አቅም፣ በ2018 ዓ.ም ወደ 428 ሺህ ቶን ከፍ ብሏል። በአሳ ምርት፦ የውሃ አካላትንና ሰው ሰራሽ ኩሬዎችን በአግባቡ በመጠቀም የተከናወነው የአሳ ጫጩት ስርጭት፣ ከ300 ሺህ ወደ 16 ነጥብ 5 ሚሊዮን አድጓል። ይህ ውጤት ሀገሪቱ በእንስሳት ተዋጽኦ ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም በጥቂት ዓመታት ውስጥ እንዴት ማጎልበት እንደተቻለ በግልጽ ያሳያል። ዘርፉ ለውጭ ምንዛሪ ግኝት ምን አበረከተ?፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የሀገር ውስጥ የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢትዮጵያ ከእንስሳት ተዋፅኦ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ አስቻይ ሁኔታዎችን ፈጥሯል። በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ብቻ 24 ነጥብ 2 ሺህ ቶን የተቀነባበረ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን ለዓለም አቀፍ ገበያ በማቅረብ 128 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል። ማጠቃለያ፦ በዘርፉ የተመዘገበውን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ አርብቶ አደር እና አርሶ አደሩ ከተለመደው ባህላዊ የእንስሳት አረባብ ዘዴ ለማላቀቅ የተጀመሩ ስራዎችን ማስቀጠል፣ የእንስሳት መኖ አቅርቦትንና ጤና አገልግሎትን የማዘመን፣ እንዲሁም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅና የማምረት አቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው። በተጨማሪም የመንግስት፣ የግሉ ዘርፍ እና የማህበረሰቡን ቅንጅት ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አሰራር መዘርጋት፣ የቴክኖሎጂ ድጋፍ ያለው የገበያ ትስስር መፍጠርና የደላሎችን ጣልቃ ገብነት ማስወገድ እንዲሁም አምራቹና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ለተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ጠንካራ መሰረት ማኖር ይቻላል። በአጠቃላይ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የግብርና እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ ሀገራዊ ብልፅግና ለመቀየር የተጀመረ ውጤታማ መንገድ መሆኑን ባለፉት አራት ዓመታት አሳይቷል። ይህ ከተጠናከረ ሀገሪቱ የምግብ ሉአላዊነቷን ለማረጋገጥ ያለመችውን ትልም ከማሳካት የሚያስቆማት ነገር እንደማይኖር አመላካች ነው።
ትንታኔዎች
የኢትዮጵያዊያን ምክክር፤ የጋራ ነገን የሚያሻግር የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ድልድይ
Jul 22, 2026 400
በሚኪያስ ጎቡ መግቢያ፡- ሀገራት ከጦርነት በላይ የሚፈትናቸው ጠላት አለ፤ እርሱም በአንድ ሀገር ልጆች መካከል የሚፈጠረው የመተማመን መሰናክል ነው። መሣሪያ የፈጠረውን ጉዳት እንደገና መገንባት ይቻላል። የተሰበረ ልብና የጠፋ መተማመን ግን በጉልበት አይመለስም። ለዚህም ነው ብዙ ሀገራት ከግጭት በኋላ ወደ ምክክር የሚመለሱት። ብሔራዊ ምክክር የአንድ መንግሥት ፕሮጀክት ወይም የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአንድ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፈው የሰላም ውርስ ነው። የሚጋጩ ሃሳቦች በጠመንጃ ሳይሆን በቃል ሲገናኙ፣ የተለያዩ ትርክቶች በመደማመጥ ሲቀራረቡ፣ ልዩነቶችም የጥላቻ ምንጭ ሳይሆኑ የመግባባት መነሻ ሲሆኑ ነው እውነተኛ ሀገራዊ ምክክር የሚፈጸመው። የዓለም ተሞክሮ እንደሚያሳየው ብሔራዊ ምክክር አንድ ዓይነት ቀመር የለውም። እያንዳንዱ ሀገር በታሪኩ፣ በባህሉ፣ በፖለቲካዊ እውነታውና በማኅበራዊ መዋቅሩ መሰረት የራሱን መንገድ ይመርጣል። ነገር ግን የሁሉም ግብ አንድ ነው፤ ግጭትን በመግባባት፣ ጥላቻን በመተማመን፣ ፍርሃትን በተስፋ መተካት። በአውሮፓ ከኮሙኒዝም ውድቀት በኋላ፣ በአፍሪካ ከአምባገነናዊ አስተዳደሮች ሽግግር ወቅት፣ በደቡብ አሜሪካ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሂደቶችና በዓረቡ ዓለም ከፖለቲካ አብዮቶች በኋላ የተካሄዱ ምክክሮች አንድ ትልቅ ትምህርት ይሰጣሉ። ምክክር ሲታመን ሀገር ያድናል፤ ለፖለቲካ ጥቅም ሲውል ግን ቀውስን ያባብሳል። ይህ የኢትዮጵያም ትልቁ ፈተና ነው። ሀገራዊ ምክክር የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት ነው። የምንናገረው ቃል፣ የምንጽፈው ሐሳብ፣ የምናዳምጠው አቋምና የምንቀበለው ልዩነት የነገዋን ኢትዮጵያ ይቀርጻሉ። ምክክር የሚጀምረው በአዳራሽ ሳይሆን በሰዎች ልብ ውስጥ ነው፤ የሚሳካውም ከመናገር በላይ በመደማመጥ ሲቻል ነው። ስለዚህ የዛሬው ጥያቄ "ምክክር ይካሄድ ወይ?" የሚል አይደለም። "ምክክሩን ለሀገር የሚበጅ፣ ለትውልድ የሚተርፍ፣ ለታሪክ የሚያስከብር እንዴት እናድርገው?" የሚለው ነው። መልሱም በአካታችነት፣ በእውነት፣ በመከባበርና በሀገርን ከግል ጥቅም በላይ በማስቀደም ውስጥ ይገኛል። ምክክር፤ የሀገር መድኃኒት ወይስ የትውልድ ፈተና? ምክክር ለምን ያስፈልጋል?፡- ማንኛውም ሀገር የሚያድገው በሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ግንባታ ብቻ አይደለም። በሕዝቦቿ መካከል በሚኖረው መተማመን ጭምር እንጂ። መንገድ፣ ድልድይና ፋብሪካ መገንባት ይቻላል፤ ነገር ግን የተሰበረ ማኅበራዊ ትስስር ካልተጠገነ የልማቱ መሠረት ይናወጣል። ስለዚህ ብሔራዊ ምክክር የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን የሀገር የወደፊት ዕጣ ፋንታ የሚወሰንበት የጋራ አስተሳሰብ ሂደት ነው። የምክክሩ ዋና ዓላማ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር አይደለም። ይልቁንም ሁሉም ወገኖች የራሳቸውን እውነት እየገለጹ፣ የሌላውንም እውነት በማዳመጥ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ሂደት ነው። እውነተኛ የምክክር ድል የሚለካውም የማን ሃሳብ አሸነፈ ሳይሆን ለሀገር ምን ያህል ሰላምና መተማመን ፈጠረ በሚለው ነው። የዓለም ተሞክሮ የሚያስተምረን፡- የታሪክ ገጾች እንደሚያሳዩት ሀገራት የብሔራዊ ምክክርን መንገድ የመረጡት ሌሎች አማራጮች ሲያቅቷቸው ነው። አንዳንዶቹ የረዥም ጊዜ የፖለቲካ ቀውስ ነበራቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በሥልጣን ሽኩቻ ተከፋፍለው ሲራኮቶ የሰነባበቱ ናቸው። ነገር ግን የተሳካላቸው ሀገራት አንድ የጋራ መርህ ነበራቸው፤ የሀገርን ጥቅም ከፓርቲ፣ ከቡድንና ከግል ጥቅም በላይ አስቀድመዋል። ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ወደ ዴሞክራሲ የተሸጋገረችው በበቀል ሳይሆን በሰለጠነ ምክክር ነው። ፖላንድና ሀንጋሪ የፖለቲካ ሽግግራቸውን በየጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር አሳልፈዋል። ላይቤሪያና ሊባኖስ የጦርነት ቁስላቸውን ለማዳን የመደማመጥን መንገድ መርጠዋል። በተቃራኒው ግን ምክክርን ለፖለቲካ ሕጋዊነት ማግኛ፣ ለሥልጣን ማራዘሚያ ወይም ለውጭ ጫና ማስታገሻ ብቻ ያደረጉ ሀገራት የበለጠ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። ይህም አንድ ግልጽ ትምህርት ይሰጠናል፤ የምክክር ስኬት የሚወሰነው በመድረኩ ሳይሆን በተመካካሪዎች ቅንነት መሆኑን ያስረዳናል። ምክክር የሚጠይቀው ከባድ ኃላፊነት፡- ሀገራዊ ምክክር የኮሚሽን ወይም የመንግሥት ሥራ ብቻ አይደለም። የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነትን የሚጠይቅ የጋራ ነገ አሻጋሪ ድልድይና የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ነው። ፖለቲከኛው የሀገርን ጥቅም ማስቀደም፣ የሚዲያው እውነትን በሚዛናዊነት ማቅረብ፣ የሲቪክ ማኅበራት የተገለሉ ድምፆችን ማሰማት፣ የኃይማኖት ተቋማት ይቅርታና መቻቻልን ማስፋፋት፣ ወጣቱ ከጥላቻ ይልቅ ውይይትን መምረጥና ምሁራን በማስረጃ የተደገፈ ሃሳብ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ማንም ወገን የራሱን አቋም ብቻ ለማስገደድ ከሞከረ፣ ምክክሩ ወደ ክርክር ይቀየራል። ሁሉም ለመረዳት እንጂ ለማሸነፍ ካልመጡ ደግሞ የምክክሩ መንፈስ ይጠፋል። የሀገራዊ ምክክር ትልቁ ድል የሌላውን አቋም መለወጥ ሳይሆን፣ የሌላውን ህመም መረዳት ነው። ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር፤ ልዩነታቸው ምንድን ነው?፡- ብዙ ጊዜ ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር የሚሉት ቃላት በአንድ ትርጉም ይጠቀሳሉ። ነገር ግን በፖለቲካዊና በማኅበራዊ ሂደቶች እያንዳንዳቸው የተለየ ዓላማና ባህሪ አላቸው። ይህንን ልዩነት አለማወቅ ሀገራዊ ምክክርን ከመጀመሪያው ሊያዛባው ይችላል። ውይይት የሐሳብ ልውውጥ ነው። ሰዎች ስለ አንድ ጉዳይ አመለካከታቸውን ይገልጻሉ፣ ይደማመጣሉ። ሁልጊዜ ውሳኔ ላይ ላይደርስ ይችላል። ክርክር የሚያተኩረው የማን ሃሳብ ትክክል እንደሆነ ላይ ነው። የራስን አቋም በማስረጃ ለማስረዳት ይደረጋል፤ አንድ አሸናፊና አንድ ተሸናፊ ሊኖር ይችላል። ድርድር ደግሞ የጥቅም ግጭትን በመካከለኛ መፍትሔ ለመፍታት የሚደረግ ሂደት ነው። እያንዳንዱ ወገን ከአቋሙ በመቀነስ የጋራ መፍትሔ ለማግኘት ይሞክራል። ሀገራዊ ምክክር ግን ከእነዚህ ሁሉ የላቀ ሂደት ነው። ዓላማው ማንንም ማሸነፍ ወይም ማስሸነፍ ሳይሆን የሀገር የወደፊት አቅጣጫ ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። በምክክር ውስጥ የሚሸነፍ ሰው የለም፤ የሚያሸንፈው ሀገር ነው። የኢትዮጵያ ልዩ እውነታ፡- ኢትዮጵያ ሦስት ሺህ ዘመናትን የተሻገረ በሕብር ያሸበረቀ ታሪክ፣ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና ኃይማኖት ያላት ሀገር ናት። ይህ በሕብር ያሸበረቀ ልዩነት የኢትዮጵያ ጥንካሬ መሆን ሲገባው በተለያዩ ወቅቶች የፖለቲካ አለመግባባቶችና የታሪክ ትርክቶች የመከፋፈል መሣሪያ ሆነው ቆይተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ፈተናም ይህ ነው። ሁሉም የራሳቸውን ታሪክ ይዘው ወደ ጠረጴዛው ይመጣሉ፤ ነገር ግን ከጠረጴዛው የሚወጡት አንድ የጋራ የወደፊት ርዕይ ይዘው መሆን አለባቸው። ይህ ቀላል አይደለም። ስለዚህ ምክክሩ ከቃላት በላይ በተግባር የሚገለጥ ቅንነትን ይፈልጋል። የዋናው ምክክር ጉባኤ የህዝብ ወኪል ተመካካሪዎችም ሀገርን የማስቀደም ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ስኬታማ ምክክር የሚመሰረትባቸው አምስት ምሰሶዎች፡- ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን ቢያንስ አምስት መሠረታዊ ምሰሶዎች ሊኖሩት ይገባል። እነሱም መተማመን፣ አካታችነት፣ እውነት፣ ፍትሕና የጋራ ርዕይ ናቸው። ከሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበራሰብ የሕዝብ ወኪል 4 ሺ ተመካካሪ ኢትዮጵያዊያንም በሀገር ግንባታ ጉዳይ፣ የመንግስት አደረጃጃትና ስርአት ጉዳይ፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬድዋ ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና የመልካም አስተዳዳር ጉዳዮች፣ የሰላም ግንባታ ጉዳዮች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽ ማዕከል እየመከሩ ይገኛል። ሀገራዊ ምክክር ያለፈውን ለመቁጠር ሳይሆን፣ የወደፊቱን ለመገንባት የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው። የኢትዮጵያ መንገድም የልዩነት ግድግዳን የሚያፈርስ የትውልድ አደራና የብሔራዊ መግባባት ማሰሪያ ጥበብና ትልም ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፤ የተገኙ ዕድሎች፣ ዋና ፈተናዎች እና የወደፊት አቅጣጫ በታሪክ ጉዞዋ ውስጥ ኢትዮጵያ ብዙ የፈተና ዘመናትን አልፋለች። አንዳንዶቹ ፈተናዎች ከውጭ ጥቃት የመጡ ቢሆኑም፣ አብዛኞቹ ግን ከውስጣዊ አለመግባባቶች፣ ከተለያዩ የታሪክ ትርክቶች፣ ከፖለቲካ ፉክክርና ከመተማመን እጥረት የተፈጠሩ ናቸው። ስለዚህ የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት የዛሬን ችግር ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፣ የትውልድ ዕዳን ለማቃለል የተጀመረ ታሪካዊ ሂደት ነው። ይህ ሂደት ቀላል አይደለም። በርካታ ዓመታት የተከማቹ ቅሬታዎች፣ የተለያዩ እውነታዎች፣ የተቃራኒ ትርክቶችና የተለያዩ የፖለቲካ ፍላጎቶች በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መገናኘታቸው በራሱ ትልቅ ፈተና ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ ትልቁ ፈተና ልዩነትን ወደ መግባባት መቀየር ነው። ዕድሎች፤ ሊጠቀሙባቸው የሚገቡ ወሳኝ መስኮቶች፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ የምታነሳበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። የታሪክ አተረጓጎም፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የሥልጣን ክፍፍል፣ የሀብት አጠቃቀም፣ የፍትሕ ጉዳዮችና የአብሮነት ዕሴቶች በጦርነት ሳይሆን በሐሳብ የሚፈቱበት ዕድል ይፈጥራል። ከዚህም በላይ ምክክሩ የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር የሚያስችል ዕድል ነው። ለብዙ ዓመታት "አሸናፊና ተሸናፊ" በሚለው አስተሳሰብ የተመራውን ፖለቲካ ወደ "አብሮ ማሸነፍ" የሚሸጋግር ከሆነ እውነትም የኢትጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ ጠንካራ መሠረት ያገኛል። በሂደቱ ፊት የሚቆሙ ፈተናዎች፡- ማንኛውም ሀገራዊ ምክክር ከፍተኛ ተስፋ እንደሚፈጥር ሁሉ ከባድ ፈተናዎችንም ይዞ ይመጣል። የመጀመሪያው ፈተና የመተማመን እጥረት ነው። ለብዙ ዓመታት የተገነባ ጥርጣሬ በጥቂት ወራት አይጠፋም። ስለዚህ የምክክሩ ተዓማኒነት በእያንዳንዱ እርምጃ ሊገነባ ይገባል። ሁለተኛው ፈተና የተለያዩ የታሪክ ትርክቶች ናቸው። አንድ ክስተት በአንዱ ወገን የድል ታሪክ ሲሆን፣ በሌላው ወገን የመከራ ታሪክ ሊሆን ይችላል። ይህን ልዩነት በክብር መቀበል እንጂ መግፋት አይቻልም። በሌላ መልኩም የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ ስርጭት ነው። በዲጂታል ዘመን አንድ ያልተረጋገጠ መረጃ በጥቂት ደቂቃዎች ሺዎችን ሊደርስ ይችላል። ስለዚህ የሚዲያ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሚወስዱት ኃላፊነት ከመቼውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። የምሁራንና የመገናኛ ብዙኅን ሚና፡- በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ምሁራን ስሜትን ሳይሆን ማስረጃን ማቅረብ አለባቸው። የማኅበረሰብ ችግሮችን በሳይንሳዊ ጥናት መተንተን፣ ከሌሎች ሀገራት ልምድ መማርና አማራጭ መፍትሔዎችን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። መገናኛ ብዙኅንም በዚህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው። መገናኛ ብዙኅን ወሬን ከማባዛት ይልቅ እውነትን ማጣራት፣ ልዩነትን ከማባባስ ይልቅ መግባባትን ማጎልበት፣ ስሜትን ከማቀጣጠል ይልቅ እውነታን ማቅረብ አለበት። ምክክሩን የሚያጠናክር የመገናኛ አውታር ታሪክ ይሠራል፤ የሚያደናቅፍ ደግሞ በታሪክ ይጠየቃል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ቀን የሚጠናቀቅ ክስተት አይደለም። ምክክር በትውልድ የሚገነባ የፖለቲካ ባህል ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራውን ሊጨርስ ይችላል፤ ነገር ግን የመደማመጥ ባህል በሕዝብ ውስጥ ካልሰረጸ የምክክሩ እውነተኛ ዓላማ አይሳካም። የዛሬ ውሳኔ፤ የነገ ኢትዮጵያ፡- አንዳንድ የታሪክ ወቅቶች በየቀኑ አይመጡም። አንዳንድ ውሳኔዎችም የአንድ መንግሥት ዘመንን ብቻ ሳይሆን የትውልዶችን ዕጣ ፈንታ ይወስናሉ። ሀገራዊ ምክክር የእነዚህ ታሪካዊ ውሳኔዎች አንዱ ነው። ዛሬ በምንመርጠው የምክክር ባህል፣ በምንገነባው መተማመንና በምናሳየው የፖለቲካ ብስለት ላይ የነገዋን የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ተምሳሌት ኢትዮጵያ ያንፃል። ምክክር ሁሉንም ችግር በአንድ ጊዜ የሚፈታ አስማታዊ መፍትሔ አይደለም። ነገር ግን ጦርነትን ከውይይት፣ ጥላቻን ከመቻቻል፣ መከፋፈልን ከመተባበር የሚተካ ብልህ መንገድ ነው። የሚያደርገውም ልዩነቶችን ማጥፋት ሳይሆን ልዩነቶችን በአንድ ሀገር ጣሪያ ስር እንዴት እንደሚኖሩ የጋራ ሕግና ሥርዓት መፍጠር ነው። በእርግጥ ኢትዮጵያ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፋለች። የፖለቲካ አለመተማመን፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የፀጥታ ችግሮች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎችና የማኅበራዊ ስብራቶች በቀላሉ የሚያልፉ አይደሉም። ይሁን እንጂ እነዚህን ችግሮች በጥይት ከመፍታት ይልቅ በምክክር ለመፍታት መሞከር በራሱ የታሪክ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ ግን የአንድ ተቋም ብቻ አይደለም። የመንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኅን ተቋማት፣ የምሁራን፣ የወጣቶች፣ የሴቶችና የእያንዳንዱ ዜጋ የጋራ ኃላፊነት ነው። የሀገር ዕጣ ፋንታ ለአንድ ቡድን ብቻ የሚተው አይደለም፤ በጋራ የሚገነባ እንጂ። ከምክክር ወደ ባህል፡- ምክክሩ ተጠናቀቀ ማለት የሀገሪቱ ችግሮች ተፈቱ ማለት አይደለም። እውነተኛው ስኬት የሚለካው የመደማመጥ ባህል በማኅበረሰቡ ውስጥ ሲሰርጽ ነው። በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመገናኛ ብዙኅን፣ በፖለቲካ ተቋማትና በየቤቱ የመነጋገር ባህል ካልጠነከረ፣ ምክክሩ የሰነድ ውጤት ብቻ ሆኖ ይቀራል። የእውነተኛ ዴሞክራሲ መሠረት ተመሳሳይ አስተሳሰብ መኖር አይደለም፤ የተለያዩ አስተሳሰቦችን በሰላም የመቀበል ባህል መኖር ነው። ልዩነት የችግር ምንጭ ሳይሆን የጥንካሬ ምንጭ ሲሆን ነው አንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም የምታገኘው። የማጠቃለያ፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚያስፈልገው ብልህ አመራር ብቻ አይደለም፤ ታጋሽ ዜጎችንም ይፈልጋል። ሀገር የምትገነባው በግንብ ሳይሆን በመተማመን ነው። ሰላም የሚጸናውም በፍርሃት ሳይሆን በፍትሕ ነው። ዛሬ የምንመርጠው የምክክር መንገድ ነገ ለልጆቻችን የምንተወው ታሪክ ይሆናል። ስለዚህ በኢትዮጵያን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተደራጅተው የሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የዛሬ አጀንዳ ብቻ አይደሉም፤ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚቀርጽ የትውልድ አደራ እንጂ። የዋናው ምክክር ጉባኤ ተመካካሪ የሕዝብ ወኪሎችም ከግልና ቡድን ፍላጎት ይልቅ የቀጣዩን ትውልድና ሀገርን ማስቀደም ይጠበቅባቸውል። ምክክር የቃላት ልውውጥ ብቻ አይደለም፤ የተሰበረ መተማመንን የሚጠግን፣ የተከፋፈለ ማኅበረሰብን የሚያቀራርብ፣ የትውልድ ታሪክን በአዲስ ተስፋ የሚጽፍ ሀገራዊ ጥበብ ነው። የምንወስነው ዛሬ የምንወርሰውን ነገ ይበይናል። ምክክር የሀገር መድኅን ነው፤ ኢትዮጵያም እየመከረች ነው።
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 573
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 4556
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 3699
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 10753
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 20924
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 13957
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 19710
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 7100
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 4882
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።