በአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ የሚሳተፉ ልዑካን አዲስ አበባ መግባት ጀመሩ - ኢዜአ አማርኛ
በአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ የሚሳተፉ ልዑካን አዲስ አበባ መግባት ጀመሩ
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦በ49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ለመሳተፍ የአፍሪካ ሀገራት ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል።
በዚሁ መሠረት የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ዶክተር ኤድዋርድ ቢዚማና አዲስ አበባ ገብተዋል።
አምባሳደር ዶክተር ኤድዋርድ ቢዚማና ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ሹም መላኩ በዳዳ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ከሐምሌ 21 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በጉባኤው ለመሳተፍ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች እና የልዑካን ቡድን አባላትም አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ።