ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በአማራ ክልል ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Mar 9, 2026 43
ባህርዳር፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ ክልላዊ የግብርና ምርምር ስራዎች አውደ ጥናት በባህር ዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ደረጀ ማንደፍሮ በወቅቱ እንደገለጹት የ25 ዓመት የአሻጋሪ ዕድገትና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር ተገብቷል። በመሆኑም በክልሉ የሚገኙ እምቅ አቅሞችን ለማልማት በሚደረገው ጥረት ተመራማሪዎች፣ ምሁራንና ተባባሪ አካላት በተቀናጀ መልኩ መስራት ይኖርብናል ብለዋል። በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የምርምር ስራዎች አማካይ የሰብል ምርትማነት በሄክታር ከ10 ኩንታል ወደ 32 ኩንታል ማደጉን ጠቅሰው በተለይም የስንዴ ምርታማነት ከፍተኛ ማንሰራራት እያሳየ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት የሚያሳድጉና ችግሮችን የሚፈቱ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በምርምር አበረታች ውጤቶች ቢመዘገብም የአፈር አሲዳማነት፣ የግብርና መካናይዜሽን ዕጥረት፣ የድህረ ምርት ብክነትና ሌሎች ችግሮች እየተፈቱ መሄድ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሰማኽኝ አስረዴ(ዶ/ር)፤ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ዓመታት የአርሶ አደሩን ኑሮ ሊቀይሩ የሚችሉ ዘርፈ ብዙ የምርምር ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። በዚህም በሰብልና እንስሳት ልማት፤ በአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ በደን ልማት ስኬታማ ውጤቶች መገኘታቸውን አንስተው በምግብ ሳይንስና በባዮ ቴክኖሎጂ የተገኙ ውጤቶችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ ግብርናውን ለማዘመን አሁን ላይ 960 የተለያዩ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አንስተው 371 የሚሆኑትን ዘንድሮ ለማጠናቀቅ መታቀዱን ተናግረዋል። የአማራ ክልል የዩኒቨሲቲዎች ፎረም ዋና ጸሀፊ ተወካይ ጀጃው ደማሙ(ዶ/ር)፤ በበኩላቸው ከግብርና ምርምርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የአርሶ አደሩን ኑሮ የሚቀይሩና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው አንስተዋል።
ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው
Mar 9, 2026 63
ወልቂጤ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በግብርናው ዘርፍ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ በወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዝርያቸው የተሻሻሉ ጊደሮችና ኮርማዎችን ለሞዴል አርሶ አደሮችና በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት የማስተላለፍ እና የመስክ ምልከታ መርሃ ግብር አካሂዷል። በወቅቱም የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ድሪባ ገለቴ(ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ በሀገሪቱ በ23 የምርምር እና በ712 የአገልግሎት ማዕከላት አዳዲስ የምርምር ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በሀገሪቱ አሁን ላይ ከ271 በላይ የምርምር ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባለፈ የሀገሪቱን እድገት ማፋጠን የሚያስችሉ በሳይንሳዊ ምርምር የተደገፉ ዘርፈ-ብዙ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህም ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል እና የእንስሳት እና ዓሳ ሃብት ዘርፍ ኃላፊ ኢያሱ ተረፈ በግብርና ምርምር የተገኘው ስኬትና ማንሰራራት ቀጣይነት እንዲኖረው የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት በክልሉ የወተት ምርታማነት 675 ሚሊየን ሊትር ላይ መድረሱን ጠቁመው በዘንድሮ ዓመት 744 ሚሊየን ሊትር ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። ኢንስቲትዩቱ በሚያከናውናቸው የምርምር ስራዎች በዞኑ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የገለፁት ደግሞ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ ናቸው። የለውጡ መንግስት ለግብርና ልማት በሰጠው ትኩረት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተግባራዊ መደረጉ የእንስሳት ልማቱን በግብዓትና በአዳዲስ አሰራር ለማገዝ አስችሏል ብለዋል። የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ቤተል ነክር በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚያስችሉ የተለያዩ የግብርና ምርምር ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰዋል። ለዓመታት የምርምርና ብዜት ሥራ ሲከናወንባቸው የነበሩ የተሻሻሉ የኮርማ፣ የጊደርና የዶሮ ዝርያዎችን ለሞዴል አርሶ አደሮች እና በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት እንዲሰጡ መደረጉንም ተናገረዋል። የሶዶ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር አድማሱ ግዛው፤ ከእርሻ ሥራቸው ጎን ለጎን ዝርያቸው የተሻሻሉ የወተት ላሞቹን በማርባት ከሚያገኙት ምርት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ገቢያቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በምርምር ማእከሉ የተሰጧቸው ዝርያቸው የተሻሻሉ ዶሮዎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያሳድግላቸው የገለፁት ደግሞ በአበሽጌ ወረዳ የጣጤሳ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ መውደድ ሰርጉ ናቸው። በወልቂጤ ከተማ ዝርያቸው የተሻሻሉ ከብቶችን በማርባት በቀን 60 ሊትር ወተት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ያነሱት ደሳለኝ ዘበርጋ(ዶ/ር) ናቸው። በዘንድሮ ዓመትም ከምርምር ማእከሉ ዝርያቸው የተሻሻሉ ጊደሮችን ማግኘታቸውን ነው የገለጹት።
በምዕራብ ወለጋ ዞን የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ነው
Mar 9, 2026 32
ጊምቢ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን ተግባራዊ የተደረጉ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ መምጣታቸውን የዞኑ አስተዳዳር ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ ለኢዜአ እንዳሉት በዞኑ በግብርና ዘርፍ ተግባራዊ የተደረጉ ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ናቸው። በዞኑ ከሰላም ማሰፈን ሥራ ጎን ለጎን የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰጠው ትኩረት በተለይ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ውጤታማ ሥራዎች እንደተከናወኑ ገልጸዋል። በመርሀግብሩ ተጠቃሚነት ለማሳደግም ዘንድሮ ከ116 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሩ ለማሰራጨት ታቅዶ እስካሁን ድረስ 99 ሺህ 375 የንብ ቀፎ ተሰራጭቷል ብለዋል። በንብ ማነብ ሥራው 15 ሺህ አርሶ አደሮች መሰማራታቸውንና በዓመቱ መጨረሻም 12 ሺህ ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን አቶ ተሊላ ጠቁመዋል። እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለጻ፣ ከንብ ማነብ ሥራ በተጨማሪ የወተት ላሞችን ዝርያ ለማሻሻል እና ለሥጋና እንቁላል ጣይ ዶሮዎች ስርጭት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። የሰብል ልማት ምርታማነትን ለማሳደግም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በግብርና ቴክኖሎጂ የመደገፍና የማስፋፋት ሥራ ተከናውኗል። በዞኑ ያለውን የመስኖ አቅም በማሳደግ አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት የማላቀቅና የሜካናይዜሽን እርሻ ልማትን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ተሊላ አመልክተዋል። በዘንድሮ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዞኑ ከ199 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ጠቁመው፣ ከዚህም 7 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል። የስንዴ ልማቱ በኩታገጥም እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት አቶ ተሊላ፣ ይህም አርሶ አደሮች ለሰብላቸው በጋራ ክትትልና እንክብካቤ በማድረግ የተሻለ ምርት እንዲገኝ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል። ከስንዴ ልማቱ በተጨማሪ ከ20 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ገበያ ተኮር የሆኑ አትክልቶች እየለሙ መሆኑንም አስረድተዋል። ከአትክልት ልማቱም 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው አቶ ተሊላ የገለጹት። በመስኖ ልማቱ ከ134 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸው፣ በዞኑ የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትናና ሉአላዊነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ በጊ ወረዳ ነዋሪ ሱሌማን ሞሐመድ እና ኑሩ ከላሜ በማህበር ተደራጅተው በሁለት ሄክታር መሬት ላይ በሚያከናውኑት ጥምር ግብርና ተጠቃሚ ሆነዋል። በመስኖ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ አትክልቶች በማልማት ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ መመረጧ የስኬታማ የልማት ጉዞ ማሳያ ነው
Mar 9, 2026 47
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናን እንድታስተናግድ መመረጧ በሁሉም መስኮች እያስመዘገበች ለምትገኘው የልማት ሥራዎች ውጤት ማሳያ መሆኑን ታዋቂ አትሌቶች ገለጹ። ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጪው ሚያዚያ ወር የሚካሄድ ዓለም አቀፍ ውድድርን እንድታዘጋጅ በዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተመርጣለች፡፡ በውድድሩ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ አትሌቶች የሚሳተፉበት ከመሆኑ ባሻገር በውድድሩ አሸናፊ የሚሆኑ አትሌቶች ከፍተኛ ሽልማት የሚያገኙበት ይሆናል። የኢትዮጵያን መመረጥ ተከትሎ ኢዜአ ያነጋገራቸው ታዋቂ አትሌቶች እንደገለጹት፤ ይህ አጋጣሚ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ መክፈቱንና ሀገሪቱን በዓለም አቀፍ መድረክ የበለጠ ለማስተዋወቅ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። የአጭር ርቀት አትሌቷ ፋንቱ ሚጌሶ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ውድድርን እንድታዘጋጅ መመረጧ በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተናግራለች፡፡ ለዚህ ስኬት ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች፣ በተለይም የስታዲየሞች፣ የመሮጫ ትራኮችና የከተማው መሰረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ጠቁማለች። ቀደም ሲል በሌሎች ሀገራት ስንሮጥ የምናየው ምቹ ሁኔታ፣ ዛሬ በሀገራችን እየተፈጠረ መሆኑን ገልጻ፤ ባለፉት ዓመታት በከተማ የታየው ለውጥ አስደናቂ መሆኑን ገልጻለች። ሌላዋ የረጅም ርቀት አትሌት መሰሉ መልካሙ፣ አዲስ አበባ ውድድሩን የማዘጋጀት ዕድል ማግኘት ለአትሌቲክሱ ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ በተጨማሪ ሀገርን ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል እንደሚፈጥር አስታውቃለች። መንግሥት በተለያዩ አካባቢዎች እየገነባቸው ያሉ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች የስልጠና ማዕከላት የመሮጫ ትራኮች ለአትሌቶች ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ መሆኑን አንስታለች፡፡ ይህ ሁኔታ ለልምምድ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረ አንስታ በአትሌቲክሱ ለሚመዘገበው ውጤት የላቀ ድርሻ እንደሚኖረውም ጨምራ ተናግራለች። የስልጠና ቦታዎችን ይበልጥ በማስፋፋት በረጅም ርቀት የምናስመዘግበውን ውጤት በአጭር ርቀት ለመድገም በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አትሌቶቹ በአስተያየታቸው አመልክተዋል። ለዚህ ደግሞ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እየተደረጉ ያሉ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም ነው የጠቆሙት።
የገጠር ኮሪደር ሥራው በአካባቢው በተገኙ ቁሳቁሶች፤ በኅብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወነ የአነስተኛ መንደር ሞዴል ክንውን ነው
Mar 9, 2026 48
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል ሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ ውስጥ የተሠራው የገጠር ኮሪደር ሥራ በአካባቢው በተገኙ ቁሳቁሶች፤ በኅብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወነ የአነስተኛ መንደር ሞዴል ክንውን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ተናገሩ ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሃረሪ ክልል የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት የአካባቢው ነዋሪ በንቃት የተሳተፈበት የገጠር ኮሪደር ሥራ ባሕላዊ የግንባታ ዘዴን፣ የተደራጀ እቅድ እና ተግባራዊ የአሰራር ውጤት ያሳየ ነው ብለዋል።
ፖለቲካ
በክልሉ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሰራ ነው
Mar 9, 2026 56
ባህር ዳር፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች በመራጭነት፣ በተመራጭነትና በታዛቢነት የሚያደርጉትን ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል - የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የክልሉ ሴቶች በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑና የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ የማንቃት ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ። ሴቶች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅማቸውን የሚያስከብርና ፍላጎታቸውን የሚያሟላ የፖለቲካ ፓርቲን ለይተው እንዲመርጡ ለማስቻል ግንዛቤያቸውን የማሳደግ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በተመራጭነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግም ውጤታማና ሞዴል የሆኑ ሴቶች በፈለጉት ፓርቲ ተመልምለው እንዲሳተፉ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውንም አመልክተዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሴቶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ በቢሮው በኩል ይህንኑ ታሳቢ ያደረጉ የተለያዩ የንቅናቄ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ዕድሜያቸው ለመምረጥ የደረሱ ሁሉም ሴቶች የምርጫ ካርዳቸውን በመውሰድ የሚፈልጉትን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ አስገንዝበዋል።
አብን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ ይገኛል- በለጠ ሞላ (ዶ/ር)
Mar 9, 2026 80
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ የሚያስችለውን ዝግጅት እያከናወነ እንደሚገኝ የአብን ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለስኬታማነቱ በቅንጅት እየተሠራ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሠረት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። በምርጫ ቦርድ እውቅና የተሰጣችው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ምልክቶቻቸውንና ማኒፌስቶዎቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ዕጩዎቻቸውን በማስመዝገብ የምርጫ ክርክር እያካሄዱ ነው። በተጨማሪም ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የመራጮች ምዝገባ ሂደት በይፋ ተጀምሯል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፣ አብን ካለፈባቸው በርካታ ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ወጥቶ አሁን ላይ ራሱን ለውድድር እያዘጋጀ ይገኛል። አብን በምርጫው ለመሳተፍ የሚያደርገው ጥረት በአማራ ክልል ብቻ የተገደበ ሳይሆን፣ በተለያዩ አካባቢዎች ጭምር ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በመሆኑም ፓርቲው በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ደጋፊዎቹን በማስተባበርና ድርጅታዊ መዋቅሩን በማጠናከር በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ ለመሆን በትኩረት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል። ምርጫው ስኬታማና ተዓማኒ እንዲሆን መንግሥት፣ ሕዝቡና የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራና በቅንጅት በመስራት የሚጠበቅባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል። በተለይም መንግሥት ሁሉም ፓርቲዎች በነፃነት የሚንቀሳቀሱበት ምቹና አስተማማኝ የፖለቲካ ምህዳር መፍጠሩን እንዲያጠናክር አንስተዋል። መገናኛ ብዙኃንም ለሁሉም ተፎካካሪ ኃይሎች እኩልና ፍትሐዊ የሆኑ የብሮድካስት መድረኮችን በማመቻቸት የድርሻቸውን ሊያበረክቱ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። እነዚህ የተቀናጁ ጥረቶች ኢትዮጵያ ወደ ላቀ የዴሞክራሲ ሥርዓት እንድትሸጋገር ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖራቸውም ሊቀመንበሩ አብራርተዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሐሳብ ልዕልናን በማስቀደም ተጨባጭና ለሀገር የሚጠቅሙ አማራጭ ዕቅዶቻቸውን ለመራጩ ሕዝብ ማቅረብ እንዳለባቸው ተናግረዋል። ፓርቲያቸው አሁን ላይ የተፈጠሩትን የፖለቲካ ዕድሎች በአግባቡ በመጠቀም፣ ሂደቱ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅበትን ድርጅታዊ ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የሚያስችለንን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል-ነዋሪዎች
Mar 8, 2026 127
ነጌሌ ቦረና ፤የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፡- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምጻቸውን ለመስጠት ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን በምስራቅ ቦረና ዞን የነጌሌ ቦረና ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባሰቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከትናንት የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ መጀመሩ ይታወሳል። በዚሁ መርሃ ግብር መሰረት ኢዜአ በነጌሌ ቦረና ከተማ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኛቸውን ነዋሪዎች አነጋግሯል። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ጉራቻ ጃተኒ በሰጡት አስተያየት በመጪው ግንቦት በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ከወዲሁ ተዘጋጅተዋል። ለዚህም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ጠቅሰው ድምጻቸውንም ለሀገር ልማትና እድገት ይሰራል ብለው ላመኑበት ፓርቲ እንደሚሰጡ ተናግረዋል። የጎቢቻ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ቱራ ሊበን በበኩላቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ የዜግነትና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ እንደወሰዱ ተናግረዋል። ምርጫ የሀገረ መንግሥት ግንባታን ለማጽናት ወሳኝ በመሆኑ እዚህ ላይ አተኩሮ ለሚሰራ ፓርቲ ድምጼን እሰጣለሁ ብለዋል። ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የአከባቢያቸውን ሠላም ነቅተው በመጠበቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም አስታውቀዋል። ሌላኛው የመራጭነት ካርድ መውሰዱን የሚናገረው የከተማው ነዋሪ ወጣት ማሙሽ ፈይሳ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች የሚተላለፈውን የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር በአግባቡ በመከታተል ለሚደግፈው ፓርቲ ድምጹን ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታውቋል። ክርክሩ የመራጭነት ካርድ ለመውሰድና በምርጫው ለመሳተፍና ድምጽ ለመስጠት እንዳነሳሳውም አክሏል። የነገሌ ምርጫ ክልል አስተባባሪ አቶ አባይነህ ወርቁ በዞኑና በነጌሌ ቦረና ከተማ በሚገኙ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ በሰላማዊ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። የመራጮች የምዝገባ ሂደቱንም 167 የምርጫ አስተባባሪዎች በቅርበት እየተከታተሉት ሲሆን 668 ምርጫ አስፈጻሚዎችም ምዝገባውን እያስፈጸሙ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።።
ብሔራዊ ጥቅምን ለታሪካዊ ጠላቶች አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ባለድርሻ አካል ሊሆኑ አይገባም - በለጠ ሞላ (ዶ/ር)
Mar 8, 2026 156
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ብሔራዊ ጥቅምን ለታሪካዊ ጠላቶች አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ አውድ ውስጥ ባለድርሻ አካል ሊሆኑ እንደማይገባ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲ ሊቀ መንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲ ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በወቅታዊ ጉዳዮች፣ በቀይ ባህርና የባህር በር ጥያቄ፣ ምርጫ 2018 በተመለከተና በሌሎች ጉዳዮች ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገው ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ቀይ ባህር ያለ ኢትዮጵያ ህዝብ ፈቃድና ይሁንታ በፖለቲካ ሴራ ያጣነው የተፈጥሮ ሃብታችን ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተፈጥሯዊ፣ ህጋዊ እና መልክዓምድራዊ መብቷን መሰረት ያደረገ ሲሆን፣ ይህንን ታሪካዊ ሀብት ማጣት በአሁኑ ትውልድ ዘንድ ከፍተኛ የቁጭት ስሜት ፈጥሯል። መንግስት ይህንን የህዝብ ጥያቄ ለመመለስና ኢትዮጵያ ያላትን ስትራቴጂካዊ ጥቅም ለማስከበር የተለያዩ ዲፕሎማሲያዊ ስልቶችን በመከተል ረጅም ርቀት ተጉዟል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ሊቀ መንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ለኢትዮጵያ የዓባይ ውሃና ቀይ ባህር ስትራቴጂካዊ ጥቅሞቿ ናቸው። ኢትዮጵያ የቀይ ባህርን ምንም ዓይነት ህጋዊ መሰረት በሌለው አግባብ በሴራ እንድታጣው መደረጉን አንስተው፤ ይህ በሁሉም ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመ ታላቅ በደል ነው ብለዋል። ከዚህ አኳያ መንግስት የባህር በር ጥያቄን ሀገራዊ አጀንዳ አድርጎ ማምጣቱን አብን በአዎንታ የሚቀበለውና የሚደግፈው አካሄድ መሆኑንም ገልጸዋል። በወቅቱ በድፍረት የተወሰነ የፖለቲካ ውሳኔ በሁሉም ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመ ታሪካዊ በደልና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ የሰጠ ታሪካዊ ስህተት እንደሆነም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በታሪክና በተፈጥሮ ያላትን የባህር በር የማግኘት መብት ዳግም የሚያረጋግጥላት ምቹ ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ የገለጹት ሊቀመንበሩ፤ አብንም ይህንን ፍትሃዊ ጥያቄ ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። ስለሆነም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለታሪካዊ ጠላቶች አሳልፈው ለመስጠት የሚሰሩ የፖለቲካ ኃይሎች በፖለቲካው አውድ ውስጥ ባለድርሻ አካል መሆን እንደሌለባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የዓባይ ውሃ ለኤሌትሪክ ሃይል ማመንጫነት በመገደብ ተጠቃሚነቷን በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ማረጋገጧን አንስተው፤ የባህር በር ጥያቄ ላይም በጋራ መስራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል። ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያ የልማት ጥረቶቿ እንዲደናቀፉ ሌት ተቀን እንደሚሰሩ ያመለከቱት ሊቀ መንበሩ፤ ኢትዮጵያውያን ግን የጋራ ጠላቶቻቸውን ሴራ በፅናት የመከቱበት ፕሮጀክት ነው ብለዋል። አሁን ላይ ከእነዚህ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች በላይ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ሌላ ምንም ዓይነት አጀንዳ እንደሌለ አረጋግጠዋል።
የትግራይ ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል -ምሁራን
Mar 8, 2026 136
ቦንጋ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ክልል ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ በሀገር ደረጃ እየተመዘገበ ካለው ሁሉን አቀፍ ልማትና ሰላም ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባው መግለፃቸው ይታወቃል። ለክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ልማትና ተጠቃሚነት መንግስት ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህወሃት ቡድን ለሌላ ጦርነት እየሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያ በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ትምህርት ክፍል መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ያሬድ አያሌው (ዶ/ር)፣ የተራማጅነት እሳቤ የሌለው የህወሃት ቡድን ዘመኑን ለሚመጥን የፖለቲካ እሳቤ ዝግጁነት የሌለው መሆኑን ባለፉት ዓመታት ማየት ተችሏል ብለዋል። ይህም በመሆኑ በተለይም የትግራይ ክልልና ህዝቡ የለውጡ ተጠቃሚ እንዳይሆን መሰናክል ሆኗል ሲሉ ጠቅሰዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን ያለውን የጸና አቋም የገለጹበት መሆኑን አንስተው፣ የህወሃት ቡድን ከዚህ በተቃራኒ ቆሞ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም የህወሃትን ቡድን ያረጀ አስተሳሰብ ለመቀየር በተለይም የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ተነሳሽነት ወስዶ መንቀሳቀስ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የህወሃት ቡድን የትግራይን ሕዝብ በተለይም ወጣቱን ሀይል እንደማሲያዣ በመጠቀም አሁን እንደሀገር እየተመዘገበ ካለው የልማት፣ የሰላምና የአንድነት ጉዞ ተነጥሎ እንዲኖር እያደረገው መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የጥፋት ቡድኑን በቃ ሊለው ይገባል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ ወደ ሰላሙ እንዲመለስ እና የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጽኑ ፍላጎት እንዳለው ያሳያል ያሉት ዶክተር ያሬድ ፤ ህዝቡም የመንግስትን ጥረት ደግፎ ለለውጥ መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የህወሃትን ቡድን እኩይ ዓላማ ማክሸፍ የሚችለው ጠንካራ ትብብርና ፅኑ ትግል ማድረግ እንዳለበት ጠቁመው፤ ይህንን ለማድረግ ጊዜ ማባከን አይገባም ብለዋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ አዲሱ ፍሪንጆ (ዶ/ር) ፤ እንዳሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልሉ ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም እጦት ምክንያት ለይተው ለዘላቂ ሰላም ጠቃሚ ናቸው ያሏቸውን ሃሳቦች ማንሳታቸው ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። የትኛውም የፖለቲካ አስተሳስብ ከዘመኑ ጋር ተራማጅ መሆኑን ያነሱት ምሁሩ፣ የህወሃት ቡድን ተቀባይነት በሌለውና በቆየ አስተሳሰብ ዛሬም እቀጥላለሁ ማለቱ የማይለወጥና ቆሞ ቀርነቱን ያሳያል ብለዋል። ባረጀ አስተሳሰቡ ቀደም ሲል በፈጠረው ግጭት የትግራይ ክልል ህዝብ ከልማት እንዳይጠቀም ማደረጉን አስታውሰው፣ ሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ በተለይ ወጣቱ ቡድኑን ሌላ ግጭት አንፈልግም ሊለው ይገባል ብለዋል። ወጣቶች ሁሌም ለሰላም ሊቆሙ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክትና ማብራሪያ ከትግራይ ክልል ነባራዊ ሁኔታ ባሻገር የኢትዮጵያን የፖለቲካ አካሄድና ሥርዓት ያሳየ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በርሁን ናቸው። ይህም ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸው፤ በተለይ የትግራይ ወጣቶች በአረጀ አስተሳሰብ ከተቸነከረው የህወሃት ቡድን ራሱን በማላቀቅ ለክልሉ ሰላምና የተሻለ አማራጭ መቆም እንዳለበት ገልጸዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ አለባቸው - ምሁራን
Mar 8, 2026 178
አሶሳ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነምግባርን በማክበር በሃሳብ ብቻ መከራከርን በመልመድ ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸውየአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ። 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማከናወን የዕጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ይገኛል። በምርጫው ዜጎች የተሻለ ሃሳብ እና ፖሊሲ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እንዲያስችላቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮችን እያከናወኑ መሆናቸው ይታወቃል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን እንደተናገሩት፤ ምርጫን በህገ መንግስቱ መሠረት በተያዘለት ገደብ ማከናወን አንዱ የዴሞክራሲ መገለጫ ነው። በዩኒቨርሲቲው የፌዴራሊዝም መምህር ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮች ህብረተሰቡ ስለሚመርጠው ፓርቲ የተሻለ ግንዛቤ እንዲይዝ ያደርጋሉ ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን በነፃነት እያከናወኑት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት የሚያግዝ እና የፓርቲዎች ማኒፌስቶ ለመራጮች ተደራሽ እንዲሆን ያግዛል ነው ያሉት። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅሰቀሳ ወቅት የሚያነሱት የምረጡኝ ቅስቀሳ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት ያለው መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነምግባርን በማክበር በሃሳብ ብቻ መከራከርን መልመድ አለባቸው ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ፤ ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ጠቅሰዋል። ሌላው በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህር አበበ አኖ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ምርጫ ለአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሔ ያመጣል ተብሎ ስለሚጠበቅ የዜጎችን ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዜጎች አሳሳች የሆነ አስተሳሰብ እንዳይዙ በማድረግ ግልፅ ፖሊሲና በምርጫው ቢያሸንፉ ሊፈጽሙት በሚገባው ትክክለኛ ፖሊሲ ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል - የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 124
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ይጠቅመናል ያልነውን ለመምረጥ የምርጫ ካርዳችንን መውሰዳቸውን በአዲስ አበባ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያካሄድ አስታውቋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም መግለጹ ይታወሳል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ተጀምሯል። የኢዜአ ሪፖርተሮች በከተማዋ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች በመዘዋወር የመራጮች የምዝገባ ሂደት ቅኝት አድርገዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ዮሀንስ አሰፋ እንደተናገረው፤ ምርጫ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ የእድገትና የልማት ጉዞ የሚያሸጋግር ፓርቲ የምንመርጥበት ኹነት ነው። ስለሆነም ኢትዮጵያን በልማት ሊያሳድግና ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያደርስ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ብሏል። ዕድሜው ለመራጭነት የደረሰ ሁሉ ምርጫ ካርድ በመውሰድ በንቃት መሳተፍ እንዳለበት አመልክቷል። በጠቅላላ ምርጫ ለሀገር ይበጃል የምለውን ለመምረጥ የምርጫ ካርዱን መውሰዱን የተናገረው ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ ኤልዔዘር ደጉ ነው። ወጣቶች ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም መምረጥ እንዲችሉ ምርጫ ካርዳ እንዲወስዱም ጥሪ አቅርቧል። በጉለሌ ክፍለ ከተማ የመራጭነት ካርድ የወሰዱት አቶ ወርቁ ይርጋው በበከላቸው፤ ኢትዮጵያን ለወደፊት የሚመራና ወደ ተሻለ የዕድገት ደረጃ ሊያሻግር የሚችል ፓርቲ ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ ምርጫ ለሰላምና ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስፈላጊ በመሆኑ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የተናገሩት ደግሞ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ነዋሪዋ ወይዘሮ አማረች በሱፍቃድ ናቸው፡፡ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ነዋሪ ወጣት እንደሻው ነጋሽ በበኩሉ፤ በመጪው ጊዜ ለዕድገት የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ በመወሰዴ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡ የዘንድሮ ምርጫ በዲጂታል የታገዘ መሆኑ ታአማኒነትን የሚጨምርና የተለያዩ መረጃ መጣረሶችን የሚያስቀር መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Mar 7, 2026 146
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተባባሪነት የተዘጋጀው ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' የተሰኘ መጽሐፍ ምረቃ መርሃ ግብር በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል። በመጽሐፉ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት፤ መጽሀፉ በሀሳብም ሆነ በይዘት የተሳካለት የታሪክ ካስማ ነው ብለዋል። በ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ላይ ታሪክ ሊይዛቸው የሚገቡ ቁምነገሮች መካተታቸውን ገልጸዋል። መጽሐፉ ታሪክ የዘነጋቸውን የዓድዋ ጀግኖች በቅጡ በመዘከር ለማስታወስ ያደረገው ጥረትም የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። የመጽሐፉ ጽንሰ ሃሳባዊ ቁምነገሮችም የኢትዮጵያዊነትን መንፈስ የሚያሰርጽ ለአዲስ ተስፋና ምኞት የሚያነሳሳ የታሪክ ሰነድ መሆኑን አንስተዋል። ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ዛሬን የምንሰራበትና ነገን የምንከተልበት ኃያል መነጽር መሆኑን አስረድተዋል። የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ መጽሐፉም የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ፋይዳ አመላክቷል ብለዋል። መጽሐፉም የዕውቀት ማስፋፊያ፣ የጎደለ መሙያ፣ ራስን መፈተሻ፣ ራስን ለመመርመር የሚያነሳሳና ምክንያታዊ እሳቤን የሚያጎለብት ሰነድ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ፖለቲካ
በክልሉ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሰራ ነው
Mar 9, 2026 56
ባህር ዳር፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች በመራጭነት፣ በተመራጭነትና በታዛቢነት የሚያደርጉትን ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል - የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የክልሉ ሴቶች በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑና የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ የማንቃት ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ። ሴቶች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅማቸውን የሚያስከብርና ፍላጎታቸውን የሚያሟላ የፖለቲካ ፓርቲን ለይተው እንዲመርጡ ለማስቻል ግንዛቤያቸውን የማሳደግ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በተመራጭነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግም ውጤታማና ሞዴል የሆኑ ሴቶች በፈለጉት ፓርቲ ተመልምለው እንዲሳተፉ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውንም አመልክተዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሴቶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ በቢሮው በኩል ይህንኑ ታሳቢ ያደረጉ የተለያዩ የንቅናቄ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ዕድሜያቸው ለመምረጥ የደረሱ ሁሉም ሴቶች የምርጫ ካርዳቸውን በመውሰድ የሚፈልጉትን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ አስገንዝበዋል።
አብን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ ይገኛል- በለጠ ሞላ (ዶ/ር)
Mar 9, 2026 80
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ የሚያስችለውን ዝግጅት እያከናወነ እንደሚገኝ የአብን ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለስኬታማነቱ በቅንጅት እየተሠራ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሠረት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። በምርጫ ቦርድ እውቅና የተሰጣችው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ምልክቶቻቸውንና ማኒፌስቶዎቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ዕጩዎቻቸውን በማስመዝገብ የምርጫ ክርክር እያካሄዱ ነው። በተጨማሪም ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የመራጮች ምዝገባ ሂደት በይፋ ተጀምሯል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፣ አብን ካለፈባቸው በርካታ ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ወጥቶ አሁን ላይ ራሱን ለውድድር እያዘጋጀ ይገኛል። አብን በምርጫው ለመሳተፍ የሚያደርገው ጥረት በአማራ ክልል ብቻ የተገደበ ሳይሆን፣ በተለያዩ አካባቢዎች ጭምር ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በመሆኑም ፓርቲው በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ደጋፊዎቹን በማስተባበርና ድርጅታዊ መዋቅሩን በማጠናከር በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ ለመሆን በትኩረት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል። ምርጫው ስኬታማና ተዓማኒ እንዲሆን መንግሥት፣ ሕዝቡና የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራና በቅንጅት በመስራት የሚጠበቅባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል። በተለይም መንግሥት ሁሉም ፓርቲዎች በነፃነት የሚንቀሳቀሱበት ምቹና አስተማማኝ የፖለቲካ ምህዳር መፍጠሩን እንዲያጠናክር አንስተዋል። መገናኛ ብዙኃንም ለሁሉም ተፎካካሪ ኃይሎች እኩልና ፍትሐዊ የሆኑ የብሮድካስት መድረኮችን በማመቻቸት የድርሻቸውን ሊያበረክቱ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። እነዚህ የተቀናጁ ጥረቶች ኢትዮጵያ ወደ ላቀ የዴሞክራሲ ሥርዓት እንድትሸጋገር ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖራቸውም ሊቀመንበሩ አብራርተዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሐሳብ ልዕልናን በማስቀደም ተጨባጭና ለሀገር የሚጠቅሙ አማራጭ ዕቅዶቻቸውን ለመራጩ ሕዝብ ማቅረብ እንዳለባቸው ተናግረዋል። ፓርቲያቸው አሁን ላይ የተፈጠሩትን የፖለቲካ ዕድሎች በአግባቡ በመጠቀም፣ ሂደቱ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅበትን ድርጅታዊ ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የሚያስችለንን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል-ነዋሪዎች
Mar 8, 2026 127
ነጌሌ ቦረና ፤የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፡- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምጻቸውን ለመስጠት ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን በምስራቅ ቦረና ዞን የነጌሌ ቦረና ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባሰቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከትናንት የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ መጀመሩ ይታወሳል። በዚሁ መርሃ ግብር መሰረት ኢዜአ በነጌሌ ቦረና ከተማ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኛቸውን ነዋሪዎች አነጋግሯል። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ጉራቻ ጃተኒ በሰጡት አስተያየት በመጪው ግንቦት በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ከወዲሁ ተዘጋጅተዋል። ለዚህም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ጠቅሰው ድምጻቸውንም ለሀገር ልማትና እድገት ይሰራል ብለው ላመኑበት ፓርቲ እንደሚሰጡ ተናግረዋል። የጎቢቻ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ቱራ ሊበን በበኩላቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ የዜግነትና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ እንደወሰዱ ተናግረዋል። ምርጫ የሀገረ መንግሥት ግንባታን ለማጽናት ወሳኝ በመሆኑ እዚህ ላይ አተኩሮ ለሚሰራ ፓርቲ ድምጼን እሰጣለሁ ብለዋል። ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የአከባቢያቸውን ሠላም ነቅተው በመጠበቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም አስታውቀዋል። ሌላኛው የመራጭነት ካርድ መውሰዱን የሚናገረው የከተማው ነዋሪ ወጣት ማሙሽ ፈይሳ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች የሚተላለፈውን የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር በአግባቡ በመከታተል ለሚደግፈው ፓርቲ ድምጹን ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታውቋል። ክርክሩ የመራጭነት ካርድ ለመውሰድና በምርጫው ለመሳተፍና ድምጽ ለመስጠት እንዳነሳሳውም አክሏል። የነገሌ ምርጫ ክልል አስተባባሪ አቶ አባይነህ ወርቁ በዞኑና በነጌሌ ቦረና ከተማ በሚገኙ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ በሰላማዊ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። የመራጮች የምዝገባ ሂደቱንም 167 የምርጫ አስተባባሪዎች በቅርበት እየተከታተሉት ሲሆን 668 ምርጫ አስፈጻሚዎችም ምዝገባውን እያስፈጸሙ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።።
ብሔራዊ ጥቅምን ለታሪካዊ ጠላቶች አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ባለድርሻ አካል ሊሆኑ አይገባም - በለጠ ሞላ (ዶ/ር)
Mar 8, 2026 156
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ብሔራዊ ጥቅምን ለታሪካዊ ጠላቶች አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ አውድ ውስጥ ባለድርሻ አካል ሊሆኑ እንደማይገባ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲ ሊቀ መንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲ ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በወቅታዊ ጉዳዮች፣ በቀይ ባህርና የባህር በር ጥያቄ፣ ምርጫ 2018 በተመለከተና በሌሎች ጉዳዮች ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገው ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ቀይ ባህር ያለ ኢትዮጵያ ህዝብ ፈቃድና ይሁንታ በፖለቲካ ሴራ ያጣነው የተፈጥሮ ሃብታችን ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተፈጥሯዊ፣ ህጋዊ እና መልክዓምድራዊ መብቷን መሰረት ያደረገ ሲሆን፣ ይህንን ታሪካዊ ሀብት ማጣት በአሁኑ ትውልድ ዘንድ ከፍተኛ የቁጭት ስሜት ፈጥሯል። መንግስት ይህንን የህዝብ ጥያቄ ለመመለስና ኢትዮጵያ ያላትን ስትራቴጂካዊ ጥቅም ለማስከበር የተለያዩ ዲፕሎማሲያዊ ስልቶችን በመከተል ረጅም ርቀት ተጉዟል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ሊቀ መንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ለኢትዮጵያ የዓባይ ውሃና ቀይ ባህር ስትራቴጂካዊ ጥቅሞቿ ናቸው። ኢትዮጵያ የቀይ ባህርን ምንም ዓይነት ህጋዊ መሰረት በሌለው አግባብ በሴራ እንድታጣው መደረጉን አንስተው፤ ይህ በሁሉም ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመ ታላቅ በደል ነው ብለዋል። ከዚህ አኳያ መንግስት የባህር በር ጥያቄን ሀገራዊ አጀንዳ አድርጎ ማምጣቱን አብን በአዎንታ የሚቀበለውና የሚደግፈው አካሄድ መሆኑንም ገልጸዋል። በወቅቱ በድፍረት የተወሰነ የፖለቲካ ውሳኔ በሁሉም ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመ ታሪካዊ በደልና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ የሰጠ ታሪካዊ ስህተት እንደሆነም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በታሪክና በተፈጥሮ ያላትን የባህር በር የማግኘት መብት ዳግም የሚያረጋግጥላት ምቹ ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ የገለጹት ሊቀመንበሩ፤ አብንም ይህንን ፍትሃዊ ጥያቄ ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። ስለሆነም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለታሪካዊ ጠላቶች አሳልፈው ለመስጠት የሚሰሩ የፖለቲካ ኃይሎች በፖለቲካው አውድ ውስጥ ባለድርሻ አካል መሆን እንደሌለባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የዓባይ ውሃ ለኤሌትሪክ ሃይል ማመንጫነት በመገደብ ተጠቃሚነቷን በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ማረጋገጧን አንስተው፤ የባህር በር ጥያቄ ላይም በጋራ መስራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል። ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያ የልማት ጥረቶቿ እንዲደናቀፉ ሌት ተቀን እንደሚሰሩ ያመለከቱት ሊቀ መንበሩ፤ ኢትዮጵያውያን ግን የጋራ ጠላቶቻቸውን ሴራ በፅናት የመከቱበት ፕሮጀክት ነው ብለዋል። አሁን ላይ ከእነዚህ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች በላይ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ሌላ ምንም ዓይነት አጀንዳ እንደሌለ አረጋግጠዋል።
የትግራይ ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል -ምሁራን
Mar 8, 2026 136
ቦንጋ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ክልል ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ በሀገር ደረጃ እየተመዘገበ ካለው ሁሉን አቀፍ ልማትና ሰላም ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባው መግለፃቸው ይታወቃል። ለክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ልማትና ተጠቃሚነት መንግስት ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህወሃት ቡድን ለሌላ ጦርነት እየሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያ በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ትምህርት ክፍል መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ያሬድ አያሌው (ዶ/ር)፣ የተራማጅነት እሳቤ የሌለው የህወሃት ቡድን ዘመኑን ለሚመጥን የፖለቲካ እሳቤ ዝግጁነት የሌለው መሆኑን ባለፉት ዓመታት ማየት ተችሏል ብለዋል። ይህም በመሆኑ በተለይም የትግራይ ክልልና ህዝቡ የለውጡ ተጠቃሚ እንዳይሆን መሰናክል ሆኗል ሲሉ ጠቅሰዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን ያለውን የጸና አቋም የገለጹበት መሆኑን አንስተው፣ የህወሃት ቡድን ከዚህ በተቃራኒ ቆሞ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም የህወሃትን ቡድን ያረጀ አስተሳሰብ ለመቀየር በተለይም የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ተነሳሽነት ወስዶ መንቀሳቀስ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የህወሃት ቡድን የትግራይን ሕዝብ በተለይም ወጣቱን ሀይል እንደማሲያዣ በመጠቀም አሁን እንደሀገር እየተመዘገበ ካለው የልማት፣ የሰላምና የአንድነት ጉዞ ተነጥሎ እንዲኖር እያደረገው መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የጥፋት ቡድኑን በቃ ሊለው ይገባል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ ወደ ሰላሙ እንዲመለስ እና የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጽኑ ፍላጎት እንዳለው ያሳያል ያሉት ዶክተር ያሬድ ፤ ህዝቡም የመንግስትን ጥረት ደግፎ ለለውጥ መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የህወሃትን ቡድን እኩይ ዓላማ ማክሸፍ የሚችለው ጠንካራ ትብብርና ፅኑ ትግል ማድረግ እንዳለበት ጠቁመው፤ ይህንን ለማድረግ ጊዜ ማባከን አይገባም ብለዋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ አዲሱ ፍሪንጆ (ዶ/ር) ፤ እንዳሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልሉ ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም እጦት ምክንያት ለይተው ለዘላቂ ሰላም ጠቃሚ ናቸው ያሏቸውን ሃሳቦች ማንሳታቸው ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። የትኛውም የፖለቲካ አስተሳስብ ከዘመኑ ጋር ተራማጅ መሆኑን ያነሱት ምሁሩ፣ የህወሃት ቡድን ተቀባይነት በሌለውና በቆየ አስተሳሰብ ዛሬም እቀጥላለሁ ማለቱ የማይለወጥና ቆሞ ቀርነቱን ያሳያል ብለዋል። ባረጀ አስተሳሰቡ ቀደም ሲል በፈጠረው ግጭት የትግራይ ክልል ህዝብ ከልማት እንዳይጠቀም ማደረጉን አስታውሰው፣ ሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ በተለይ ወጣቱ ቡድኑን ሌላ ግጭት አንፈልግም ሊለው ይገባል ብለዋል። ወጣቶች ሁሌም ለሰላም ሊቆሙ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክትና ማብራሪያ ከትግራይ ክልል ነባራዊ ሁኔታ ባሻገር የኢትዮጵያን የፖለቲካ አካሄድና ሥርዓት ያሳየ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በርሁን ናቸው። ይህም ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸው፤ በተለይ የትግራይ ወጣቶች በአረጀ አስተሳሰብ ከተቸነከረው የህወሃት ቡድን ራሱን በማላቀቅ ለክልሉ ሰላምና የተሻለ አማራጭ መቆም እንዳለበት ገልጸዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ አለባቸው - ምሁራን
Mar 8, 2026 178
አሶሳ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነምግባርን በማክበር በሃሳብ ብቻ መከራከርን በመልመድ ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸውየአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ። 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማከናወን የዕጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ይገኛል። በምርጫው ዜጎች የተሻለ ሃሳብ እና ፖሊሲ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እንዲያስችላቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮችን እያከናወኑ መሆናቸው ይታወቃል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን እንደተናገሩት፤ ምርጫን በህገ መንግስቱ መሠረት በተያዘለት ገደብ ማከናወን አንዱ የዴሞክራሲ መገለጫ ነው። በዩኒቨርሲቲው የፌዴራሊዝም መምህር ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮች ህብረተሰቡ ስለሚመርጠው ፓርቲ የተሻለ ግንዛቤ እንዲይዝ ያደርጋሉ ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን በነፃነት እያከናወኑት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት የሚያግዝ እና የፓርቲዎች ማኒፌስቶ ለመራጮች ተደራሽ እንዲሆን ያግዛል ነው ያሉት። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅሰቀሳ ወቅት የሚያነሱት የምረጡኝ ቅስቀሳ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት ያለው መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነምግባርን በማክበር በሃሳብ ብቻ መከራከርን መልመድ አለባቸው ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ፤ ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ጠቅሰዋል። ሌላው በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህር አበበ አኖ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ምርጫ ለአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሔ ያመጣል ተብሎ ስለሚጠበቅ የዜጎችን ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዜጎች አሳሳች የሆነ አስተሳሰብ እንዳይዙ በማድረግ ግልፅ ፖሊሲና በምርጫው ቢያሸንፉ ሊፈጽሙት በሚገባው ትክክለኛ ፖሊሲ ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል - የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 124
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ይጠቅመናል ያልነውን ለመምረጥ የምርጫ ካርዳችንን መውሰዳቸውን በአዲስ አበባ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያካሄድ አስታውቋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም መግለጹ ይታወሳል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ተጀምሯል። የኢዜአ ሪፖርተሮች በከተማዋ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች በመዘዋወር የመራጮች የምዝገባ ሂደት ቅኝት አድርገዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ዮሀንስ አሰፋ እንደተናገረው፤ ምርጫ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ የእድገትና የልማት ጉዞ የሚያሸጋግር ፓርቲ የምንመርጥበት ኹነት ነው። ስለሆነም ኢትዮጵያን በልማት ሊያሳድግና ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያደርስ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ብሏል። ዕድሜው ለመራጭነት የደረሰ ሁሉ ምርጫ ካርድ በመውሰድ በንቃት መሳተፍ እንዳለበት አመልክቷል። በጠቅላላ ምርጫ ለሀገር ይበጃል የምለውን ለመምረጥ የምርጫ ካርዱን መውሰዱን የተናገረው ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ ኤልዔዘር ደጉ ነው። ወጣቶች ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም መምረጥ እንዲችሉ ምርጫ ካርዳ እንዲወስዱም ጥሪ አቅርቧል። በጉለሌ ክፍለ ከተማ የመራጭነት ካርድ የወሰዱት አቶ ወርቁ ይርጋው በበከላቸው፤ ኢትዮጵያን ለወደፊት የሚመራና ወደ ተሻለ የዕድገት ደረጃ ሊያሻግር የሚችል ፓርቲ ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ ምርጫ ለሰላምና ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስፈላጊ በመሆኑ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የተናገሩት ደግሞ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ነዋሪዋ ወይዘሮ አማረች በሱፍቃድ ናቸው፡፡ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ነዋሪ ወጣት እንደሻው ነጋሽ በበኩሉ፤ በመጪው ጊዜ ለዕድገት የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ በመወሰዴ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡ የዘንድሮ ምርጫ በዲጂታል የታገዘ መሆኑ ታአማኒነትን የሚጨምርና የተለያዩ መረጃ መጣረሶችን የሚያስቀር መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Mar 7, 2026 146
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተባባሪነት የተዘጋጀው ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' የተሰኘ መጽሐፍ ምረቃ መርሃ ግብር በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል። በመጽሐፉ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት፤ መጽሀፉ በሀሳብም ሆነ በይዘት የተሳካለት የታሪክ ካስማ ነው ብለዋል። በ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ላይ ታሪክ ሊይዛቸው የሚገቡ ቁምነገሮች መካተታቸውን ገልጸዋል። መጽሐፉ ታሪክ የዘነጋቸውን የዓድዋ ጀግኖች በቅጡ በመዘከር ለማስታወስ ያደረገው ጥረትም የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። የመጽሐፉ ጽንሰ ሃሳባዊ ቁምነገሮችም የኢትዮጵያዊነትን መንፈስ የሚያሰርጽ ለአዲስ ተስፋና ምኞት የሚያነሳሳ የታሪክ ሰነድ መሆኑን አንስተዋል። ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ዛሬን የምንሰራበትና ነገን የምንከተልበት ኃያል መነጽር መሆኑን አስረድተዋል። የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ መጽሐፉም የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ፋይዳ አመላክቷል ብለዋል። መጽሐፉም የዕውቀት ማስፋፊያ፣ የጎደለ መሙያ፣ ራስን መፈተሻ፣ ራስን ለመመርመር የሚያነሳሳና ምክንያታዊ እሳቤን የሚያጎለብት ሰነድ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ማህበራዊ
የገጠር ኮሪደር ሥራው በአካባቢው በተገኙ ቁሳቁሶች፤ በኅብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወነ የአነስተኛ መንደር ሞዴል ክንውን ነው
Mar 9, 2026 48
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል ሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ ውስጥ የተሠራው የገጠር ኮሪደር ሥራ በአካባቢው በተገኙ ቁሳቁሶች፤ በኅብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወነ የአነስተኛ መንደር ሞዴል ክንውን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ተናገሩ ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሃረሪ ክልል የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት የአካባቢው ነዋሪ በንቃት የተሳተፈበት የገጠር ኮሪደር ሥራ ባሕላዊ የግንባታ ዘዴን፣ የተደራጀ እቅድ እና ተግባራዊ የአሰራር ውጤት ያሳየ ነው ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተጣለባቸውን ሃገራዊ ኃላፊነት በሚገባ ለመወጣት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል
Mar 9, 2026 82
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መንግሥትና ሕዝብ የጣለባቸውን ሃገራዊ ኃላፊነት ለመወጣትና ትርጉም ያለው ውጤት ለማስመዝገብ በቅንጅት ሊሠሩ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለጹ። የምገባ መርሃ ግብር በተማሪዎች ውጤት ላይ መሻሻል እንዲመጣ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው የትምህርት ሚኒስቴር ለሁለት ቀናት የሚቆይ የ2018 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቁልፍ ተግባራት ላይ የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምርምሮችን በማከናወንና ብቁ ዜጋን በማፍራት ረገድ ያላቸው ሚና የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። ተቋማቱ አሁን ካለው ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታ ጋር ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ በልዩ ትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከአመራር እስከ ታችኛው የሥራ ክፍል የተቀናጀ ርብርብ ያስፈልጋል ያሉት ሚኒስትሩ ተቋማቱ ለሃገር ዕድገት እያበረከቱ ያሉትን አስተዋጽኦ ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሸኔ በበኩላቸው፤ ተቋማቱ በሥራ ባሕልና በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ መሻሻል ማሳየታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲዎች የምርምር ሥራዎች መሻሻል እያሳዩ መሆኑን ጠቅሰው የትምህርት ተደራሽነትና አካታችነትን ከማረጋገጥ ባለፈ በምርምር ጥራት ላይ በትኩረት እንደሚሠራም ተናግረዋል፡፡ ግምገማው ተቋማቱ ከሚኒስቴሩ ጋር በገቡት ውል መሠረት ያከናወኗቸውን ተግባራት እና ያጋጠሟቸውን ፈተናዎች በጥልቀት ለመለየት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በዚህ መድረክ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ የሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የምገባ መርሃ ግብር በተማሪዎች ውጤት ላይ መሻሻል እንዲመጣ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው
Mar 9, 2026 85
ሰመራ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦ የትምህርት ቤቶች የምገባ መርሃ ግብር ማህበራዊ መረጋጋት በመፍጠር በተማሪዎች ውጤት ላይ መሻሻል እንዲመጣ አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ተናገሩ። እመርታ ቤተ-መጻሕፍት በአንድ ጊዜ ለ1 ሺህ ሰው አገልግሎት መስጠት ይችላል - የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት 11ኛው የአፍሪካ የትምህርት ቤት የምገባ መርሃ ግብር "የትምህርት ቤት ምገባ ለተማሪዎች ተሳትፎና ውጤታማነት አይተኬ ሚና አለው" በሚል መሪ ሐሳብ በሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር በአሰቦዳ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከብሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ እንደተናገሩት፤ የትምህርት ቤት የምገባ መርሃግብር ማህበራዊ መረጋጋት በመፍጠር በተማሪዎች ውጤት ላይ መሻሻል አሳይቷል። መርሃ ግብሩ በተለይም አነስተኛ የገቢ ምንጭ ላላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች እፎይታ የሰጠና የተማሪዎች የትምህርት አቀባበልና ጤንነት ላይ ለውጥ እያመጣ መሆኑንም ተናግረዋል። ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ ከማድረግ ባሻገር የትምህርት ፍላጎታቸው እንዲጨምር እያደረገ መሆኑን ነው የገለጹት። በሀገር አቀፍ ደረጃ በመርሃ ግብሩ ከ8 ሚሊዮን በላይ ህፃናት ተጠቃሚ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታዋ ተናግረዋል። የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ የመስኖ ስራን በማጠናከር መርሃ ግብሩን ለማገዝ የጀመረውን የእርሻ ስራ ሌሎች ክልሎችም በአብነት ወስደው መተግበር እንደሚገባቸው ተናግረዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአፋር ክልል ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ወጣቶች ባህልና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀሚድ ዱላ በበኩላቸው፤ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር የነገ ተስፋ የሆኑ ህፃናትን የወደ ፊት ዕጣ ፈንታ ያመቻቸ ነው ብለዋል። በተለይም እንደ አፋር ክልል በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ተግዳሮት ለሚያጋጥማቸው አካባቢዎች ምላሽ መስጠት የቻለ አዎንታዊ ፋይዳ ማበርከቱን አብራርተዋል። በመርሃ ግብሩ ለትምህርት ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በአፋር ክልል የትምህርት ምጣኔ እንዲሻሻል አስተዋፅኦ ማድረጉን ተናግረዋል። የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሳ አደም በበኩላቸው፤ የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር የተማሪዎች የመማር ፍላጎት እንዲጨምርና በተረጋጋ ሁኔታ ትምህርታቸውን መከታተል እንዲችሉ አግዟል። በአካልና አዕምሮ ዕድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኀላፊዎች፣ የግብረ ሰናይ ድርጅት ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኃይማኖት ተቋማት በሰላም ግንባታ አስተዋጿቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
Mar 9, 2026 75
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦የኃይማኖት ተቋማት የወንድማማችነት ትርክትን በማስረጽ ለሰላም ግንባታ እያበረከቱ ያለውን አስተዋጽኦ ሊያጠናክሩ ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አስታወቁ። በክልሉ ከኃይማኖት ተቋማት ጋር በትብብር በመስራት ፈጣን እድገት ለማስመዝገብ የተጀመረው ተግባር ይጠናከራል "የመደመር መንግስትና የኃይማኖት ተቋማት" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ የኃይማኖት ተቋማት የውይይት መድረክ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ ነው ። ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት፤ የኃይማኖት ተቋማት የዜጎችን ስብዕና በመቅረጽ ሀገሩን የሚወድ ትውልድ በማፍራት የጎላ ድርሻ ሲወጡ ቆይተዋል። ተቋማቱ ምዕመናንን በማስተማር ለሀገር ልማት ሚናቸዉን እንዲወጡ ማስቻላቸውንም ጠቅስዋል። የኃይማኖት ተቋማቱ በአስተምህሮቶቻቸው የወንድማማችነት ትርክትን በማስረጽ በሰላም ግንባታ እያበረከቱ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ተግባሩን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ። ተቋማቱ የዜጎች አንድነት እንዲጎለብትና ችግሮችን በውይይት የመፍታት ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማድረግ በኩል ሚናቸውን በበለጠ እንዲወጡም አመልክተዋል ። የኃይማኖት ተቋማት ሰላምና አንድነትን በማስተማር ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ልማት ያላቸዉ አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ (ረ/ፕ) ናቸዉ። ተቋማቱ ትውልድን መልካም ስብዕና በማስታጠቅ የተጣለባቸዉን አደራ ሲወጡ መቆየታቸዉንም አንስተዋል። የኃይማኖት ተቋማቱ የመደጋገፍና የመተሳሰብ ባህልን በማዳበር የህዝቡ ሰላማዊ ግንኙነት እንዲጠናከር ሲያደርጉት የነበረውን ተግባር ሊያጠናክሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ትውልድን በስነ ምግባር የማነጽና ሰላምና ፍቅር እንዲፀና የማድረግ ተግባራቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም አመልክተዋል። በመድረኩ የኃይማኖት ተቋማት ተወካዮች፣ የክልል፣ የዞን እና የከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ተመሳሳይ መድረክም በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች በመካሄድ ላይ ይገኛል ።
ኢኮኖሚ
በምዕራብ ወለጋ ዞን የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ነው
Mar 9, 2026 32
ጊምቢ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን ተግባራዊ የተደረጉ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ መምጣታቸውን የዞኑ አስተዳዳር ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ ለኢዜአ እንዳሉት በዞኑ በግብርና ዘርፍ ተግባራዊ የተደረጉ ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ናቸው። በዞኑ ከሰላም ማሰፈን ሥራ ጎን ለጎን የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰጠው ትኩረት በተለይ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ውጤታማ ሥራዎች እንደተከናወኑ ገልጸዋል። በመርሀግብሩ ተጠቃሚነት ለማሳደግም ዘንድሮ ከ116 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሩ ለማሰራጨት ታቅዶ እስካሁን ድረስ 99 ሺህ 375 የንብ ቀፎ ተሰራጭቷል ብለዋል። በንብ ማነብ ሥራው 15 ሺህ አርሶ አደሮች መሰማራታቸውንና በዓመቱ መጨረሻም 12 ሺህ ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን አቶ ተሊላ ጠቁመዋል። እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለጻ፣ ከንብ ማነብ ሥራ በተጨማሪ የወተት ላሞችን ዝርያ ለማሻሻል እና ለሥጋና እንቁላል ጣይ ዶሮዎች ስርጭት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። የሰብል ልማት ምርታማነትን ለማሳደግም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በግብርና ቴክኖሎጂ የመደገፍና የማስፋፋት ሥራ ተከናውኗል። በዞኑ ያለውን የመስኖ አቅም በማሳደግ አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት የማላቀቅና የሜካናይዜሽን እርሻ ልማትን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ተሊላ አመልክተዋል። በዘንድሮ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዞኑ ከ199 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ጠቁመው፣ ከዚህም 7 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል። የስንዴ ልማቱ በኩታገጥም እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት አቶ ተሊላ፣ ይህም አርሶ አደሮች ለሰብላቸው በጋራ ክትትልና እንክብካቤ በማድረግ የተሻለ ምርት እንዲገኝ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል። ከስንዴ ልማቱ በተጨማሪ ከ20 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ገበያ ተኮር የሆኑ አትክልቶች እየለሙ መሆኑንም አስረድተዋል። ከአትክልት ልማቱም 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው አቶ ተሊላ የገለጹት። በመስኖ ልማቱ ከ134 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸው፣ በዞኑ የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትናና ሉአላዊነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ በጊ ወረዳ ነዋሪ ሱሌማን ሞሐመድ እና ኑሩ ከላሜ በማህበር ተደራጅተው በሁለት ሄክታር መሬት ላይ በሚያከናውኑት ጥምር ግብርና ተጠቃሚ ሆነዋል። በመስኖ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ አትክልቶች በማልማት ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመን የተቀረፁ ኢንሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው
Mar 9, 2026 59
አዳማ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመን የተቀረፁ ኢንሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ። የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማፋጠን አዳዲስ የምርምር ሥራዎች እየተካሄዱ ነው በአዲስ መልክ ተከልሰው ወደ ትግበራ የገቡ የወተት ልማት፣ ዶሮ፣ ዓሣና የእንስሳት መኖ ፓኬጆች ዙሪያ በየደረጃው ለሚገኙ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአዳማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ ግብርናን ለማሻገር ከተቀረፁት ኢንሼቲቮች ውስጥ የእንስሳት ሀብት ልማትን የማዘመን ስራ አንዱ ነው። የእንስሳት ሀብቱን ውጤታማነት ለማሳደግና ዘርፉን ለማዘመን እየተተገበሩ ባሉ ኢኒሼቲቮች ተጨባጭ ውጤትና ለውጦች እየተመዘገቡ ናቸው ብለዋል። በዚህም የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ፣ የምግብና ስነ ምግብ ስርዓትን ለማስረፅ የሚደረገውን ጥረት የሚያሳኩ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን ገልፀዋል። የእንስሳት ዝርያን ለማሻሻል የተከናወኑት ተግባራት በተለይም በሰው ስራሽ ስነ ዘዴ በማዳቀል የወተት ሀብት ልማት እንዲጨምር ከማድረግ ባለፈ የተሻሻሉ ጥጆችና ጊደሮች በስፋት እንዲወለዱ ማድረጉን ነው የገለጹት። በየዓመቱም ከ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የወተት ላሞችን ማዳቀል እንደተቻለ አንስተዋል። ልዩ ዝርያ ያላቸውን የወተት ላሞችን በመደበኛና ሰው ሰራሽ ስነ ዘዴ ማዳቀልን ጨምሮ በዶሮ ፣ ዓሣና በማር ልማት ስራ የተሻለ ውጤት መምጣቱን አንስተዋል። የማር ልማት ኢንሼቲቭን ለማሳካት በየዓመቱ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎ እየተሰራጨ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የማር ምርት በዘመናዊ ቀፎ እንዲካሔድ መደረጉ ከባህላዊ ቀፎ ሲገኝ የነበረውን 10 ኪሎግራም የማይበልጥ ምርት በአማካይ 25 ኪሎግራም ለማድረስ መቻሉን ነው የተናገሩት። መድረኩ የእንስሳት ሀብት ዘርፉን ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ውጤቶችና ተሞክሮዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ግብርናን ለማሻገር የተቀመጠውን ግብ በተቀናጀ ርብርብ ለማሳካት ያለመ ነው ያሉት ደግሞ የቢሮው የእንስሳት ሀብት ልማት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ቶሌራ ደበላ ናቸው። በተጨማሪም የወተት ላሞች ልማት፣ የዶሮ፣ ዓሣ፣ ማር፣ ዓሣማና የእንስሳት መኖ ልማትን ጨምሮ በአዲስ መልክ የተከለሱ ስድስት ፓኬጆች ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥ አላማ ያነገበ ነው ብለዋል። ይህም የእንስሳት ሀብቱን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ፣ ምግብና ስነ ምግብ ስርዓትን ለማስረፅ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ እርምጃ ተወስዷል
Mar 9, 2026 67
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑ ተገለጸ። በክልሉ ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቷል የክልሉ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አፀደ አይዛ በነገው እለት የሚካሄደውን የኢንቨስትመንት ፎረም አስመልክተው ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ ለማቅረብ በመቻሉ በርካታ ባለሃብቶችን ለመሳብ እየተቻለ መሆኑን አብራርተዋል። በተያዘው በጀት ዓመት 10 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 226 ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰደው ወደ ሥራ ገብተዋል ነው ያሉት። ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ እየተካሔደ ያለው የድጋፍና የክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ኮሚሽነሯ የገለጹት። በአሁኑ ወቅትም ለኢንቨስትመንት መሬት ተረክበው ወደልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በተለዩ 81 ፕሮጀክቶች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ የተወሰደ ሲሆን 13 ሺህ 600 ሄክታር መሬት ወደ መሬት ባንክ ለማስገባት መቻሉን አስታውቀዋል። በነገው እለት የሚካሔደው የኢንቨስትመንት ፎረም ከባለሀብቶች ጋር ውይይቶችን በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተዋል። በመሆኑም ባለሀብቶች በክልሉ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ በመጠቀም በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ለሎጎ ሐይቅ ሪዞርት መዳረሻነት የሚያገለግል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተፋጠነ
Mar 9, 2026 60
ደሴ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦በሐይቅ ከተማ አስተዳደር በሚገኘው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት እየተከናወነ ያለው የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ገለፀ። በክልሉ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማት ከዘርፉ የሚገኝን ገቢ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ በአካባቢው ለቱሪዝም ዘርፉ መነቃቃት እድልን ፈጥሯል። ሪዞርቱ የአካባቢውን ፀጋ ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ከማገዙም ባለፈ ሀብቱን በዓለም ለማስተዋወቅ፣ ለዜጎች የሥራ እድል ለመፍጠርና ለከተማው እድገት አዎንታዊ ሚና እንዳለውም እሙን ነው። በሐይቁ አካባቢ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ስራዎች ላይ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ከድር መሀመድ ለኢዜአ እንዳሉት፣ በከተማው በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎች ቢኖሩም ለምተው ጥቅም መስጠት ሳይችሉ ቆይተዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት መገንባትን ተከትሎ ለሪዞርቱ መዳረሻነት የሚያገለግል መሰረተ ልማት ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከተማ አስተዳደሩ በመደበው ከ150 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው በዚህም የብስክሌት፣ የእግረኛና ሌሎች መዝናኛዎች መካተታቸውን ተናግረዋል። እንዲሁም በፌዴራል እና በክልል መንግስት በጀት ከሐይቅ ከተማ በፒያሳ አደባባይ አድርጎ እስከ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት የሚወስደው ሁለት ነጥብ አንድ ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል ብለዋል። መንገዱ ደረጃውን የጠበቀ በግራና በቀኝ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ ጭምር ያለው መሆኑንም አመልክተዋል። የሐይቅ ከተማ ነዋሪ አቶ አብዱ ሙሄ በበኩላቸው፣ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በከተማው ያሉ የታሪክ እና የገዳማት መገኛዎችን ለዓለም ያሳየ እና ለዘመናት የልማት ጥያቄዎች መልስ የሰጠ ነው ብለዋል። ሪዞርቱ የበለጠ የቱሪስት መዳረሻ እና ለጎብኚዎችም ምቹ እንዲሆን የአስፋልት መንገድና ሌሎችም የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን ገልፀዋል። የከተማዋን ሰላም በአንድነት በመጠበቅ ሪዞርቱ የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ በገንዘብና በጉልበት እያገዝን እንገኛለን ያለው ደግሞ ወጣት ሰይድ ዑመር ነው። ሪዞርቱ የተረሳውን የተፈጥሮ ፀጋ ወደ ሚጨበጥ ኢኮኖሚ የሚቀይር የልማት አሻራ በመሆኑ ተደስተናል ብሏል። የከተማው የኮሪደር ልማት እየተጠናቀቀ በመሆኑ ለሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ነው የገለጸው፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በአማራ ክልል ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Mar 9, 2026 43
ባህርዳር፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ ክልላዊ የግብርና ምርምር ስራዎች አውደ ጥናት በባህር ዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ደረጀ ማንደፍሮ በወቅቱ እንደገለጹት የ25 ዓመት የአሻጋሪ ዕድገትና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር ተገብቷል። በመሆኑም በክልሉ የሚገኙ እምቅ አቅሞችን ለማልማት በሚደረገው ጥረት ተመራማሪዎች፣ ምሁራንና ተባባሪ አካላት በተቀናጀ መልኩ መስራት ይኖርብናል ብለዋል። በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የምርምር ስራዎች አማካይ የሰብል ምርትማነት በሄክታር ከ10 ኩንታል ወደ 32 ኩንታል ማደጉን ጠቅሰው በተለይም የስንዴ ምርታማነት ከፍተኛ ማንሰራራት እያሳየ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት የሚያሳድጉና ችግሮችን የሚፈቱ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በምርምር አበረታች ውጤቶች ቢመዘገብም የአፈር አሲዳማነት፣ የግብርና መካናይዜሽን ዕጥረት፣ የድህረ ምርት ብክነትና ሌሎች ችግሮች እየተፈቱ መሄድ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሰማኽኝ አስረዴ(ዶ/ር)፤ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ዓመታት የአርሶ አደሩን ኑሮ ሊቀይሩ የሚችሉ ዘርፈ ብዙ የምርምር ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። በዚህም በሰብልና እንስሳት ልማት፤ በአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ በደን ልማት ስኬታማ ውጤቶች መገኘታቸውን አንስተው በምግብ ሳይንስና በባዮ ቴክኖሎጂ የተገኙ ውጤቶችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ ግብርናውን ለማዘመን አሁን ላይ 960 የተለያዩ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አንስተው 371 የሚሆኑትን ዘንድሮ ለማጠናቀቅ መታቀዱን ተናግረዋል። የአማራ ክልል የዩኒቨሲቲዎች ፎረም ዋና ጸሀፊ ተወካይ ጀጃው ደማሙ(ዶ/ር)፤ በበኩላቸው ከግብርና ምርምርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የአርሶ አደሩን ኑሮ የሚቀይሩና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው አንስተዋል።
ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው
Mar 9, 2026 63
ወልቂጤ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በግብርናው ዘርፍ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ በወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዝርያቸው የተሻሻሉ ጊደሮችና ኮርማዎችን ለሞዴል አርሶ አደሮችና በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት የማስተላለፍ እና የመስክ ምልከታ መርሃ ግብር አካሂዷል። በወቅቱም የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ድሪባ ገለቴ(ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ በሀገሪቱ በ23 የምርምር እና በ712 የአገልግሎት ማዕከላት አዳዲስ የምርምር ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በሀገሪቱ አሁን ላይ ከ271 በላይ የምርምር ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባለፈ የሀገሪቱን እድገት ማፋጠን የሚያስችሉ በሳይንሳዊ ምርምር የተደገፉ ዘርፈ-ብዙ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህም ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተገኙ ውጤቶችን ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል እና የእንስሳት እና ዓሳ ሃብት ዘርፍ ኃላፊ ኢያሱ ተረፈ በግብርና ምርምር የተገኘው ስኬትና ማንሰራራት ቀጣይነት እንዲኖረው የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት በክልሉ የወተት ምርታማነት 675 ሚሊየን ሊትር ላይ መድረሱን ጠቁመው በዘንድሮ ዓመት 744 ሚሊየን ሊትር ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። ኢንስቲትዩቱ በሚያከናውናቸው የምርምር ስራዎች በዞኑ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የገለፁት ደግሞ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ ናቸው። የለውጡ መንግስት ለግብርና ልማት በሰጠው ትኩረት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተግባራዊ መደረጉ የእንስሳት ልማቱን በግብዓትና በአዳዲስ አሰራር ለማገዝ አስችሏል ብለዋል። የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ቤተል ነክር በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚያስችሉ የተለያዩ የግብርና ምርምር ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰዋል። ለዓመታት የምርምርና ብዜት ሥራ ሲከናወንባቸው የነበሩ የተሻሻሉ የኮርማ፣ የጊደርና የዶሮ ዝርያዎችን ለሞዴል አርሶ አደሮች እና በዘርፉ ለተሰማሩ ማህበራት እንዲሰጡ መደረጉንም ተናገረዋል። የሶዶ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር አድማሱ ግዛው፤ ከእርሻ ሥራቸው ጎን ለጎን ዝርያቸው የተሻሻሉ የወተት ላሞቹን በማርባት ከሚያገኙት ምርት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ገቢያቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በምርምር ማእከሉ የተሰጧቸው ዝርያቸው የተሻሻሉ ዶሮዎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያሳድግላቸው የገለፁት ደግሞ በአበሽጌ ወረዳ የጣጤሳ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ መውደድ ሰርጉ ናቸው። በወልቂጤ ከተማ ዝርያቸው የተሻሻሉ ከብቶችን በማርባት በቀን 60 ሊትር ወተት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ያነሱት ደሳለኝ ዘበርጋ(ዶ/ር) ናቸው። በዘንድሮ ዓመትም ከምርምር ማእከሉ ዝርያቸው የተሻሻሉ ጊደሮችን ማግኘታቸውን ነው የገለጹት።
በድሬዳዋ አዲስ የፍተሻ ላቦራቶሪ በማደራጀት አገልግሎቱ ተደራሽ ተደርጓል
Mar 8, 2026 129
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አዲስ የፍተሻ ላቦራቶሪ ተደራጅቶ አገልግሎቱ ተደራሽ መደረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በድሬዳዋ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ድርጅቱ ዓለም አቀፍ የአሰራር ስርዓትን በመከተል ለአምራቾች፣ ለአገልግሎት ሰጪዎች፣ ለላኪዎች፣ ለአስመጪዎች፣ ለተቆጣጣሪ መስሪያ ቤቶች፣ ለምርምር ተቋማትና ለሸማቹ ማህበረሰብ የምርትና አገልግሎቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎትን እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡ በድሬዳዋ አካባቢ ለሚገኙ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ነፃ የንግድ ቀጣና እንዲሁም የደረቅ ወደብን መሰረት በማድረግ አዲስ የፍተሻ ላቦራቶሪ በማደራጀት አገልግሎቱን ተደራሽ ማድረጉን ገልፀዋል። ተቋሙ ከዚህ ቀደም በምግብ ዘይት፣ በነዳጅ ምርት፣ በተለያዩ የምግብ ምርቶች፣ ለማስዋቢያና የዲተርጀንት ምርቶች፣ ለኮንስትራክሽን ምርቶችና ግብዓቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡
ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ የዲጅታል አገልግሎትን ይበልጥ ለማስፋት አቅዶ እየሠራ ነው
Mar 8, 2026 122
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ የዲጅታል አገልግሎትን ይበልጥ ለማስፋት አቅዶ እየሠራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጎብኝተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ በውስጡ 10 ተቋማት ይዞ 73 የሚሆኑ አገልግሎቶችን ለዜጎች በመስጠት ላይ ይገኛል። አንድ ማዕከሉ ተገልጋዬችን የሚያስተናግዱ 96 ካውንተሮች እንዲኖሩት ተደርጎ የተደራጀ መሆኑንም ገልፀዋል ። ማዕከሉ ስራ ከጀመረበት ስድስት ወራቶች ውስጥ በአጠቃላይ ከ23 ሺ በላይ ተገልጋዮችን ማስተናገዱንም ተናግረዋል፡፡ ከፍ ብሎ የተጀመረውን የተቀላጠፈ የዲጅታል አገልግሎት ይበልጥ ለማስፋት አቅዶም እየሠራ ነው ብለዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ መመረጧ የስኬታማ የልማት ጉዞ ማሳያ ነው
Mar 9, 2026 47
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናን እንድታስተናግድ መመረጧ በሁሉም መስኮች እያስመዘገበች ለምትገኘው የልማት ሥራዎች ውጤት ማሳያ መሆኑን ታዋቂ አትሌቶች ገለጹ። ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጪው ሚያዚያ ወር የሚካሄድ ዓለም አቀፍ ውድድርን እንድታዘጋጅ በዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተመርጣለች፡፡ በውድድሩ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ አትሌቶች የሚሳተፉበት ከመሆኑ ባሻገር በውድድሩ አሸናፊ የሚሆኑ አትሌቶች ከፍተኛ ሽልማት የሚያገኙበት ይሆናል። የኢትዮጵያን መመረጥ ተከትሎ ኢዜአ ያነጋገራቸው ታዋቂ አትሌቶች እንደገለጹት፤ ይህ አጋጣሚ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ መክፈቱንና ሀገሪቱን በዓለም አቀፍ መድረክ የበለጠ ለማስተዋወቅ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። የአጭር ርቀት አትሌቷ ፋንቱ ሚጌሶ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ውድድርን እንድታዘጋጅ መመረጧ በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተናግራለች፡፡ ለዚህ ስኬት ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች፣ በተለይም የስታዲየሞች፣ የመሮጫ ትራኮችና የከተማው መሰረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ጠቁማለች። ቀደም ሲል በሌሎች ሀገራት ስንሮጥ የምናየው ምቹ ሁኔታ፣ ዛሬ በሀገራችን እየተፈጠረ መሆኑን ገልጻ፤ ባለፉት ዓመታት በከተማ የታየው ለውጥ አስደናቂ መሆኑን ገልጻለች። ሌላዋ የረጅም ርቀት አትሌት መሰሉ መልካሙ፣ አዲስ አበባ ውድድሩን የማዘጋጀት ዕድል ማግኘት ለአትሌቲክሱ ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ በተጨማሪ ሀገርን ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል እንደሚፈጥር አስታውቃለች። መንግሥት በተለያዩ አካባቢዎች እየገነባቸው ያሉ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች የስልጠና ማዕከላት የመሮጫ ትራኮች ለአትሌቶች ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ መሆኑን አንስታለች፡፡ ይህ ሁኔታ ለልምምድ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረ አንስታ በአትሌቲክሱ ለሚመዘገበው ውጤት የላቀ ድርሻ እንደሚኖረውም ጨምራ ተናግራለች። የስልጠና ቦታዎችን ይበልጥ በማስፋፋት በረጅም ርቀት የምናስመዘግበውን ውጤት በአጭር ርቀት ለመድገም በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አትሌቶቹ በአስተያየታቸው አመልክተዋል። ለዚህ ደግሞ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እየተደረጉ ያሉ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም ነው የጠቆሙት።
በሊጉ ነገሌ አርሲ ከባህርዳር ከተማ ፋሲል ከነማ ከምድረገነት ሽሬ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Mar 9, 2026 67
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ባህርዳር ከተማ ከነገሌ አርሲ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ባህርዳር ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው 22 ጨዋታዎች በአምስቱ አሸንፎ በአምስቱ ተሸንፎ በ12ቱ አቻ ወጥቷል። በ22ቱ ጨዋታዎች 15 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 17 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ27 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ነገሌ አርሲ በሊጉ 20 ጨዋታዎች አከናውኖ በ10ሩ ጊዜ ድል ሲቀናው በአምስቱ ተሸንፏል። ሰባት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። 22 ግቦችን ሲያስቆጥር 14 ጎሎችን አስተናግዷል። አዲስ አዳጊው ነገሌ አርሲ በ37 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ባህርዳር ከተማ ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ተሸንፏል። ተጋጣሚው ነገሌ አርሲ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ ይጫወታሉ። በሌላኛው መርሐ-ግብር ምድረ ገነት ሽሬ ከፋሲል ከነማ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ምድረ ገነት ሽሬ እስከ አሁን በሊጉ ያሸነፈው የጨዋታ ብዛት ስድስት ነው። ስምንት ጊዜ ሲሸነፍ በተመሳሳይ ስምንት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 15 ግቦችን ሲያስቆጥር 16 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ26 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው ፋሲል ከነማ በበኩሉ 22 ጨዋታዎችን አድርጎ ስምንት ጊዜ ሲያሸንፍ አምስት ጊዜ ተሸንፏል። በስምንት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 16 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 14 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ፋሲል ከነማ በ33 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ምድረ ገነት ሽሬ በ22ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር በወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የ1 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዷል። ፋሲል ከነማ ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድን ከሀዲያ ሆሳዕና በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ24 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሀዲያ ሆሳዕና በ28 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። በ22ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ መድን ከሸገር ከተማ፣ ሀዲያ ሆሳዕና ከአዳማ ከተማ በተመሳሳይ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ ይጫወታሉ። ድሬዳዋ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ። ድሬዳዋ ከተማ በ28 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ24 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ጨዋታው ድሬዳዋ ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሁለት ሽንፈቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።
የኤፍኤ ካፕ የጥሎ ማለፍ መርሐ-ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል
Mar 9, 2026 77
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡- የእንግሊዝ ኤፍኤ ካፕ ጥሎ ማለፍ (አምስተኛ ዙር) የመጨረሻ ጨዋታ ዛሬ በዌስትሃም ዩናይትድ እና ብሬንትፎርድ መካከል ይደረጋል። ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ላይ በለንደን ስታዲየም ይካሄዳል። ዌስትሃም ዩናይትድ በአራተኛው ዙር ማክስፊልድን፣ ብሬንትፎርድ በርተን አልቢዮንን በማሸነፍ ጥሎ ማለፍ ገብተዋል። ሁለቱ ክለቦች በኤፍ ካፕ ሲገናኙ የአሁኑ ለአራተኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው ሶስት ጨዋታዎች ቡድኖቹ በተመሳሳይ አንድ ጊዜ ሲያሸንፉ በቀሪው ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። እ.አ.አ በ2023 ለመጨረሻ ጊዜ በውድድሩ በነበራቸው ግንኙነት ዌስትሃም ዩናይትድ 1 ለ 0 በማሸነፍ ለአራተኛ ዙር አልፏል። ዌስትሃም ዩናይትድ ሶስት ጊዜ የኤፍኤ ካፕን ዋንጫ አንስቷል። ለመጨረሻ ጊዜ ውድድሩን ያሸነፈው እ.አ.አ በ1980 ነበር። የብሬንትፎርድ ትልቁ የኤፍኤ ካፕ ውጤት በአራት አጋጣሚዎች ለሩብ ፍጻሜ ያለፈባቸው ናቸው። የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፈው ቡድን ሩብ ፍጻሜውን የሚቀላቀል የመጨረሻው ቡድን ይሆናል። የ42 ዓመቱ አንድሪው ማድሌይ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። አርሰናል፣ ማንችስተር ሲቲ፣ ቼልሲ፣ ሊቨርፑል፣ ሊድስ ዩናይትድ፣ ሳውዝሃምፕተን እና ፖርት ቫሌ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀሉ ክለቦች ናቸው።
በተጠባቂው የደርቢ ጨዋታ ኤሲ ሚላን ኢንተር ሚላንን አሸነፈ
Mar 9, 2026 78
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ) ፦ በጣልያን ሴሪ አ የ28ኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐ- ግብር ኤሲ ሚላን ኢንተር ሚላንን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሳን ሲሮ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የክንፍ ተጫዋቹ ፔርቪስ እስቱፒናን በ35ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በጨዋታው ኢንተር ሚላን በኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢወስድም ክለቦቹ ግልጽ የግብ እድሎችን በመፍጠር ተመጣጣኝ ነበሩ። 246ኛው የሚላን ደርቢ በኢንተር ሚላን አሸናፊነት ተጠናቋል። በሊጉ 17ኛ ድሉን ያስመዘገበው ኤሲ ሚላን በ60 ነጥብ ሁለተኛ ይዟል። ከሊጉ መሪ ኢንተር ሚላን ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ዝቅ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢንተር ሚላን በ67 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ክለቦች ዋንጫውን ለማንሳት እየተፎካከሩ ይገኛል። ቡድኖቹ በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ኤሲ ሚላን በተመሳሳይ 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ አሻራ፣ የወንዝ ዳርቻ፣ የከተማና ገጠር ኮሪደር ልማት ስኬቶች ጤናማ የአካባቢ ሥነ-ምኅዳር መፍጠር አስችለዋል
Mar 9, 2026 68
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ፣ የወንዝ ዳርቻ፣ የከተማና ገጠር ኮሪደር ልማት ስኬቶች ጤናማ የአካባቢ ሥነ-ምኅዳር መፍጠር ማስቻላቸውን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ገለጸ። የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ተምሳሌታዊ ተግባር ነው የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ በሁለተኛው ዙር ፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ ፈጠራና የሕግ ተከባሪነት ስኬታማ ስራ ተሰርቷል። የአረንጓዴ አሻራ፣ የወንዝ ዳርቻ፣ የከተማና ገጠር ኮሪደር ልማት ስኬቶችም የአካባቢ ብክለትን በመቀነስ ለፅዱ ኢትዮጵያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸዋል። የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ የፕላስቲክ፣ የአፈር፣ የውሃ፣ የአየርና የድምፅ ብክለትን በመከላከል የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ላይ ትኩረት ማድረጉን ተናግረዋል። በንቅናቄው መሠረት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ15 ሚሊየን በላይ ከሚሆን ህዝብ ጋር የገፅ ለገፅ መድረክ በመፍጠር የአካባቢ ጥበቃና ፅዱ አካባቢ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መሰጠቱን አንስተዋል። በመገናኛ ብዙሃንም ከ50 ሚሊየን በላይ ህዝብ ተደራሽ በማድረግ ህብረተሰቡ በአካባቢ ላይ የሚደርስ ብክለትን መቀነስ የሚያስችል የዕውቀት፤ የግንዛቤና የሕግ ማስከበር ሥራ መሰራቱን አስረድተዋል። በዚህም በሁለት ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ የዜጎችን የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ በማሳደግ ፅዱና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችል መሰረት መጣሉን ጠቅሰዋል። በቀጣይም 3ኛ ዙር የፅዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድርግ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። በ3ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ንቅናቄም የለውጡን ዓመታትን የአረንጓዴ አሻራ፣ የወንዝ ዳርቻ፣ የከተማና ገጠር ኮሪደር ልማት ስኬቶች በማጽናት ባህል ይሰራል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተተገበሩ የአረንጓዴ አሻራ፣ የወንዝ ዳርቻ፣ የገጠርና ከተማ ኮሪደር ልማት ስኬቶች የአካባቢ ብክለትን በመቀነስ ለፅዱ ኢትዮጵያ ግንባታ ወሳኝ ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። የኮሪደር ልማት ስራ የፍሳሽ አወጋገድና የቆሻሻ አያያዝን በማዘመን ዜጎችን ፅዱ የመኖሪያ ምኅዳር በማጎናጸፍ የወንዞችን ጤናማነት የሚያስጠብቅ ተምሳሌታዊ የልማት ስኬት መሆኑንም ተናግረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃና የእርከን ሥራ የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን በማስጠበቅ ገንቢ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አንስተዋል። በሰርኩላር ኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታም ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚሰሩ የግሉን ዘርፍ ማበረታታት የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑንም አመላክተዋል።
በጋምቤላ ክልል የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Mar 9, 2026 103
ጋምቤላ ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። በክልሉ ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቷል በክልሉ በዘንድሮው ዓመት እየተካሄደ ባለው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች የማጠናከሪያ መርሃ ግብር በጎግ ወረዳ እየተካሔደ ነው። ርዕሰ መስተዳደሯ አለሚቱ ኡሞድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ፤የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጎላ ድርሻ አላቸው። ይህን ታሳቢ በማድረግ በተራቆቱ አካባቢዎች የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን በማጠናከር በክልሉ የተጀመረውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ስኬታማ ለማድረግ በትኩረት መስራቱ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የአካባቢ መራቆትንና የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል በኩል እመርታዊ ለውጥ እንዲመጣ እያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ በሁሉም አካባቢዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት ይገባዋል ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤልያስ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመላቀቅ ለተቀመጠው ግብ መሳካት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች የላቀ አበርክቶ አላቸው። ባለፉት አመታት ለተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች በተሰጠው ትኩረት የተጎዱ መሬቶች እንዲያገግሙና የግብርና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል። በመሆኑም የተፈጥሮ ሃብትን መሠረት ያደረገ የግብርና ልማትን ለማስፋት የተጀመረው ጥረት በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የጋምቤላ ክልልም ለግብርና ልማት የተመቸ ስነ ምህዳር ያለው አካባቢ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ሃብት በአግባቡ አልምቶ ከመጠቀም አንፃር የቅንጅት ስራዎች እንደሚጠናከሩ ገልፀዋል። በክልሉ ሲከናወን በቆየው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ የአፈር እርጥበታማነትንና ለምነትን በማሻሻል የሰብል ምርታማነትን እያሳደገ ይገኛል ያሉት ደግሞ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድሮው ቱት ናቸው። በክልሉ የተፋሰስ ልማትን በማጠናከር የከርሰ ምድርና የገፀ ምድርን የውሃ ሀብት በማሻሻል የግብርና ልማቱን ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት። በክልሉ በዘንድሮዉ የተፋሰስ ልማት ስራ በሁሉም ወረዳዎች በ101 ተፋሰሶች፤ 64 ሺህ ሄክታር የተራቆተ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ከቢሮው የተገኘ መረጃ ያመለክታል ።
የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከስጋት መታደግ የሚያስችል የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ ይሰራል
Mar 7, 2026 144
አርባ ምንጭ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የስምጥ ሸለቆ ተፋሰስ የሆኑ የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከስጋት ለመታደግ የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ እንደሚሰራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተባባሪነት የአባያና ጫሞ ሀይቆች የሚያስከትሉትን ተጽእኖ መቀነስ የሚያስችል የባለድርሻ አካላት ውይይት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት የአባያና ጫሞ ሀይቆችን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሉ ከፀጋነት ወደ ስጋትነት እየተቀየሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይ በጋሞ፣ በጋርዱላ፣ በኮንሶና በቡርጂ ዞኖች የሚገኙ አርሶ አደሮችን ማሳ እንዲሁም በተለያዩ መሠረተ ልማቶች ላይ አደጋ እያስከተሉ ይገኛሉ ብለዋል። በመሆኑም ሐይቆቹን ከስጋት ለመታደግ የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ እንደሚጠናከር ገልጸዋል፡፡ ተፋሰሶቹ የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር፣ የፍራፍሬ፣ የብዝሃ ህይወት የቱሪዝምና የቀጣናዊ ልማት ማሳለጫዎች መሆናቸውን ጠቅሰው ከስጋት ወደ ሀብት ምንጭነት ለመቀየር የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በውሃው ዘርፍ የረጅም ጊዜ ልምድ ያለው አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉን ችግሮች ለመቅረፍ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው የክልሉ መንግስት የበኩሉን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። የማዕድን ሚኒስትርና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በበኩላቸው የአባያና ጫሞ ሃይቆችን በዘላቂነት መጠቀም ለሃገር ሁለንተናዊ ብልጽግና ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በአርባ ምንጭና አካባቢው መልከ ብዙ ፀጋዎች መኖራቸውን ጠቅሰው የሀይቆቹን ትሩፋት ለማጉላት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በአግባቡ ሊከናወን እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተገኙ ጥናቶች መሠረት የተፋሰሶቹን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ፕሮግራሞች፣ ስትራቴጂዎችና ፕሮጀክቶች ተቀርጸው መተግበር እንዳለባቸውም አመልክተዋል። የአባያና ጫሞ ሀይቆች የውሃ መጠን መጨመር፣ የተፋሰሱ ወንዞች ሙላትና ደለል ከፍተኛ አካባቢያዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎችን እያስከተሉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አብደላ ከማል(ዶ/ር) ናቸው። የአባያና ጫሞ እንዲሁም ሌሎች ተፋሰሶች በተቀናጀ ሁኔታ ካልተመሩ ተጽዕኖው ከሀይቆቹ ዳርቻ አልፎ ሰፊ ቦታዎችን ሊያዳርስ እንደሚችል በጥናት መረጋገጡንም ጠቅሰዋል። ዩኒቨርሲቲው በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች የሚከሰቱ ተግዳሮቶችን በሳይንሳዊ መንገድ ለመከላከል የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የስራ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎችም እየተሳተፉ ነው።
የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ተምሳሌታዊ ተግባር ነው
Mar 7, 2026 98
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አርአያ የሚሆን ስራ እያከናወነች እንደምትገኝ የዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን ገለጹ። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባትና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን ማምረት፣ አረንጓዴ አሻራ፣ የስንዴ ምርታማነት፣ የኢትዮጵያ የማዳበሪያ እና የጤናማ አፈር ፍኖተ ካርታ፣ አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን የመስኖ ስራዎች ማስፋትና የተራቆቱ መሬቶችን በአካባቢ ጥበቃ ስራ ወደ ነባር ይዞታቸው መመለስ ከተከናወኑ ተግባር መካከል ይጠቀሳሉ። የዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እየገነባች ያለችው አቅም የሚደነቅ መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ስኬታማ ስራዎችን እያከናወነች እንደሚገኝ ጠቅሰው እንደ አረንጓዴ አሻራ ባሉ ኢኒሼቲቮች የቀጣናው ሀገራት ተጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የዘርፉ ስኬቶች ለማስፋት መንግስት፣ ቀጣናዊ ተቋማት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይበልጥ ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸውም አመልክተዋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በቀጣናው የሚገኙ ሀገራት በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ያላቸውን አቅም የበለጠ ማጠናከር እንደሚኖርባቸውም ነው ባለሙያው የገለጹት። በዚህ ረገድ የዓለም ባንክ ከመንግስታት ጋር የግሉ ዘርፍ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ያለውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለማሳደግና በተለይም ለወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኢኖቬሽን፣ ዲጂታል መፍትሄዎች፣ ዘላቂ የኢነርጂ አጠቃቀም እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑንም ነው ያነሱት። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የዓለም የግብርና ፋይናንስ ከፍተኛ ለውጥ ማሳየቱን ገልጸው ሀገራት ፋይናንስ በዘላቂነት የሚያመጡ አጋርነቶችን መፍጠር እንዳለባቸው መክረዋል። ለዚህ ተቋማት ትስስራቸውን ማጠናከር፣ አማራጭ ፋይናንስ መፈለግ፣ እሴት መጨመር ትኩረት መስጠት እና ለጋራ ግብ በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በቀጣናው የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው -ኢጋድ
Mar 8, 2026 77
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂን ጨምሮ በቀጣናው የሴቶችን የአመራርና ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው። "መብቶች፣ ፍትህ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሴቶችን ቀን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፏል። ኢጋድ ለሴቶች አመራር ሰጪነት፣ አይበገሬነት እና በቀጣናው ሰላም፣ ብልጽግና እና ለውጥ ለማምጣት እያበረከቱት ላለው አስተዋጽኦ ክብር እና እውቅና እንደሚሰጥ ገልጿል። በኢጋድ ሴቶች በቀጣናው አመራር ሰጪነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የኢጋድ የሰላም፣ ግብርና፣ ዲጂታል ደህንነት፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና መሬት አስተዳደር ፎረሞች እንዲሁም የኢጋድ የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂ ጨምሮ የተለያዩ ኢንሼቲቮች እየተገበረ መሆኑን አመልክቷል። የሴቶች ድምጽ እንዲሰማ እና መሉ ተሳትፏቸው እንዲረጋገጥ የሚያግዙ መድረኮችን መፍጠሩን ነው የኢጋድ ሴክሬተሪያት በመረጃው ያስታወቀው።
ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በሰላምና ደኅንነት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Mar 5, 2026 125
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢጋድ የሰላም እና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ውይይቱን ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁን (ዶ/ር) በመወከል ነው። ውይይቱ ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም፣ ደኅንነት እና መረጋጋት ላይ ያላቸውን የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው። ሁለቱ ወገኖች የጋራ የተግባር ምላሽ ለመስጠት እና ስትራቴጂካዊ ትብብራቸውን ለማጎልበት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የመንግሥታቱ ድርጅትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ ይገባል
Mar 4, 2026 222
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ እንደሚገባ ተገለጸ። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከጃፓን ኤምባሲ ጋር በመሆን የተባበሩት መንግሥታት ሪፎርም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል። የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ ቢሆኑም በተቋማዊ አወቃቀር ሥርዓት ላይ አፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ያገለሉ ናቸው። የአማኒ አፍሪካ ዳይሬክተር ሰለሞን አየለ ደርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት መዋቅር የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃ ሊወስድ ይገባል። በተቋማቱ የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥም ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ተከታታይ ሥራ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትና ከሌሎች ሀገራት ጋር ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን የዓለምአቀፍ ተቋማት ፍትሐዊ ውክልና ማስከበር የሚስችል መዋቅራዊ የሪፎርም እርምጃ እንዲወሰድ መስራት ይገባል ብለዋል። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በአፍሪካ ሕብረትና የአፍሪካ ዳያስፖራ ጉዳዮች ላይ በጥናትና ምርምር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የጋና አምባሳደር ሮበርት አፍሪይ(ዶ/ር)፤ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ያቀረበችው ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ችላ በመባሉ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ የሌላት ብቸኛ አህጉር አድርጓታል ብለዋል። ለዚህም የመንግስታቱ ድርጅት አፍሪካ በተሸከመችው የጸጥታው ምክር ቤት የሥራ ጫና ልክ ውክልና የሚያስገኛትን የሪፎርም እምርጃ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። በአፍሪካ ሕብረት የጃፓን ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኖቦሩ ሴኪጉቺ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በመንግስታቱ የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ላይ ፍትሐዊ ውክልና ሊሰጣት ይገባል ብለዋል። ጃፓንም አፍሪካ በመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የሚኖራትን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። ጃፓንና የጂ-4 አባል ሀገራት የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡም አስታውቀዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2024 በጸደቀው "የወደፊት ስምምነት" ላይ የጸጥታው ምክር ቤት መዋቅራዊ የማሻሻያ እርምጃ ለመወሰድ የተቀመጠው አቅጣጫ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቀጣናዊ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 1, 2026 186
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ እያሳደረ ባለው ከፍተኛ ተጽእኖ ምክንያት የቀጣናው የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እና የዜጎች የኑሮ መሰረት አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብ ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል።
ሐተታዎች
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 231
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 280
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 282
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 721
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 314
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 419
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1143
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1139
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3635
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2422
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8216
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6701
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 437
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 407
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።