ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ሚና ወሳኝ ነው
May 8, 2026 27
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና የአህጉሪቱን ትርክት በባለቤትነት ለመምራት የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ሚና ወሳኝ መሆኑን የፓናል ውይይት ተሳታፊዎች ገለጹ። በፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ሚዲያ እና በኤ.ጂ.ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ትብብር የተዘጋጀው የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና በድምሩ 321 ሚሊየን ተከታዮች ያሏቸው 61 ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 120 ኢትዮጵያውያን የይዘት ፈጣሪዎች አዲስ የዲጂታል ታሪክ ለመጻፍ በጉባኤው ታድመዋል። በጉባኤው ላይ "የአፍሪካን አዎንታዊ ገጽታ መገንባት" በሚል ርዕስ በተካሄደው የፓናል ውይይት፤ ታዋቂው ጋናዊ የይዘት ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር (ዎዴ ማያ) "ታሪካችንን እንዲነግሩልን ሌላ አካል መጠበቅ የለብንም" ሲል ተናግሯል። ትኩረቱን ዘወትር በአዎንታዊ ታሪኮች ላይ በማድረግ የአፍሪካን ውበት ለዓለም እያስተዋወቀ እንደሚገኝ የገለጸው ዎዴ ማያ፣ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ለውጦችን በራሱ ተነሳሽነት በቪዲዮ መዘገቡንና ስራዎቹም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘታቸውን አስታውቋል። የአፍሪካ መንግስታት ለሀገር በቀል ይዘት ፈጣሪዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አሳስቧል። የ2025 የዓለም ቆንጆ (Miss World Africa) ሀሴት ደረጀ በበኩሏ፤ አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ መድረኮች የራሳቸውን ማንነትና እሴት ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው ገልጻለች። ትክክለኛ ተፅዕኖ መፍጠር የሚቻለው የራስን ባህል፣ ቋንቋ እና እሴት ሳይሸራርፉ ለዓለም ማቅረብ ሲቻል መሆኑንም አስገንዝባለች። ከቱሪዝም ሚኒስቴር የመጡት አቶ ቴዎድሮስ ደርበው በበኩላቸው፤ መንግስት የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ቁልፍ አጋር ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የባህል መዳረሻ ብቻ ሳትሆን የወደፊት ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን ማሳየት እንደሚገባ ገልጸዋል፡ አፍሪካን በተመለከተ ሲነገሩ የነበሩ የተሳሳቱ ትርክቶችን ወደ ዕድገትና ፈጠራ ትርክት መቀየር እንደሚገባም በአጽንኦት ገልጸዋል።
የአፍሪካን እውነት ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል
May 8, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን እውነት ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች ገለጹ። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛል። ጉባኤውም ኃላፊነት የሚሰማቸው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማጠናከር፣ ትብብርን ለመፍጠርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ግብን ለማሳካት ያለመ ነው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣የአህጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶችን ለማስመዝገብና የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር የጋራ ምክክር ያደርጋሉ። በጉባኤው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፣ የኤ.ጂ.ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገመዳ ኦላና፣ የአፍሪካ ህብረት ተወካዮችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። በጉባኤው ላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ዝግጅቶች ላይ ያለውን አስተዋጽኦ የሚዳስስ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የናቹራል ላንጉዌጅ ፕሮሰሲንግ ምርምር ዲቪዥን ዳይሬክተር ሳሙኤል ራህመቶ፤ ቀደም ሲል የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለባለሙያዎች የቴክኒክና የምርምር ሥራ ይውል እንደነበር ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ የማህበረሰቡን የዕለት ተእለት የሥራ እንቅስቃሴ ቀለል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣን ዕድገትም ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ የፕሮዳክሽን ሥራዎችን የሚያከናውን ምኅዳር በመፍጠር እንደ ሲኒማ የሚታዩ ምስሎችን መፍጠር እያስቻለ መሆኑን አንስተዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምስልና ድምፅ የማመንጨት አቅም ዕድገት የይዘት ፈጣሪዎችን ሥራ እያገዘ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለይዘት ዝግጅት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለአህጉሪቱ ትርክትና ገፅታ ግንባታ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአህጉሪቱን እውነተኛ ባህልና ታሪክ ለዓለም ማህበረሰብ ለመተረክም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። ሌላኛው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ብራያን ጆታ በበኩሉ፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጠራን በማላቅ የዲጂታል ክህሎትን የሚያበለፅግ የቴክኖሎጂ አማራጭ መሆኑን ገልጿል። በዚህም የአፍሪካን እውነተኛ ገፅታ ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የዲጂታል አማራጭ ክህሎትን በማሳደግ መጠቀም እንደሚያስፈልግ ተናግሯል። ቦትስዋናዊው ታዋቂ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪ ዊሊያምላስት ኬ.አር.ኤም፤ የይዘት ፈጠራ ሥራዎችን ከገንዘብ ማግኛና ቁጥር ባሻገር ለአህጉሪቱ ትርክት ግንባታ መጠቀም አለብን ብሏል። ለዚህም የሥራ ፍቅር ባህልን በማዳበር የዲጂታል አማራጮችን የአፍሪካን የተሻለ ገፅታና ትርክት በሚያጎላ መልኩ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጿል።
የህዝብን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች የተሰጠው ትኩረት ተጠናክሮ ይቀጥላል
May 8, 2026 49
ጅማ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች ግንባታ የተሰጠው ትኩረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ነመራ ቡሊ ገለጹ። በጅማ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል። በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ነመራ ቡሊ፤ በክልሉ ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት ግብ ተጥሎ እየተሰራ ነው። ለዚህም የህዝብን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል። ባለፉት ጥቂት አመታት ሰፊ የስራ ዕድልን በመፍጠር የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰራው ስራ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት መሆኑን ጠቅሰዋል። በጅማ ከተማ የተመረቁት ፕሮጀክቶችም የዚሁ አካል ናቸው ብለዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሀ ቀመር በበኩላቸው፤ የብልፅግና ጉዟችንን እያረጋገጥን እንቀጥላለን ብለዋል። ከለውጡ በኋላ እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶች ብዛት ብቻ ሳይሆን ጥራት እና ፍጥነትንም ያማከሉ ናቸው ያሉት አቶ ጠሀ የያዝናቸውን ኢኒሼቲቮች ለማሳካት ሁሌም በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። በከተማው በዚህ አመት ከ12 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑን አመልክተዋል። በከተማው በዛሬው እለት የማምረቻ ሼዶች ፣ የዶሮ እርባታ እና የገበያ ማዕከል እንዲሁም የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ተመርቋል።
ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል የዘመኑ ብሔራዊ አርበኝነት ነው
May 8, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል የዘመኑ ብሔራዊ አርበኝነት መሆኑን የአዲስ መሶብ ዲጂታል አንድ ማዕከል አገልግሎት ሠራተኞች ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የመጀመሪያውን የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት ማስጀመራቸው ይታወቃል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት በአፍሪካ ፈር ቀዳጅ ሥራ መሆኑን ገልጸዋል። ማንኛውም ሰው በመሶብ የአንድ ማዕከል ሲገለገል ለኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥ ዕድገት ምስክርነት የሚሰጥና ብልፅግናን የሚያረጋግጥ የአርበኝት ዘመን መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል። የመጀመሪያው የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎትም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የአዲስ አበባ የከተማዋ ክፍሎች በመዘዋወር ለዜጎች ቀልጣፋና ስሉጥ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት ሰጪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዜጎች የሚገባቸውን የመንግሥት አገልግሎት ግልፅና ቀልጣፋ ማድረግ ዘመኑ የሚጠይቀው አርበኝነት ነው። ከአገልግሎት ሰጪዎቹ መካከል ዘውዱ አምሳሉ፤ ወቅቱ የሚጠይቀው የዘመኑ አርበኝነት ህዝብን በቅንነት፣ በታማንነትና ታታሪነት ማገልገል መሆኑን ገልጸዋል። የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎቱም ዜጎች በመንግሥት አገልግሎት የሚገጥማቸውን መጉላላት በማስቀረት ቅርብና ጊዜ ቆጣቢ አገልግሎት የሚያስገኝ መሆኑን ተናግረዋል። በመጀመሪያው የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸው ታላቅ ኩራትና ደስታ የሚቸር የአርበኝነት መገለጫ መሆኑን አንስተዋል። የሚሰጡት ቀልጣፋና ግልፅ አገልግሎትም የህዝብና መንግሥትን መተማመን በማጠናከር ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንዳለው አስረድተዋል። ለመዲናዋ ነዋሪዎች የተሳለጠ አገልግሎት በማቅረብ ለመጭው ትውልድ አርዓያ የሚሆን አሻራ እያሳረፉ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ሌላኛው አገልግሎት ሰጪ ኤፍሬም አሰፋ በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ተገልጋዮች የተለያዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ስር የሚያገኙበትን ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። በዘመኑ የልማት አርበኝነት ጉዞም በተሰማሩበት ሙያ ዜጎች የሚፈልጉትን የመንግሥት አገልግሎት በግልፅና ቀልጣፋ አሰራር እየሰጡ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለመዲናዋ ነዋሪዎች የሚሰጡት የተሳለጠ ሙያዊ የመንግሥት ተቋማት አገልግሎትም እንግልትን በማስቀረት እርካታን የሚሰጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ መሶብ ተንቀሳቃሽ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመጀመሪያ ዙር ሠራተኛ በመሆኔ እጅግ ደስታ ይሰማኛል ያሉት ደግሞ የማዕከሉ አገልግሎት ሰጪ ጫልቱ ታደሰ ናቸው። ተገልጋዮች ተገልግለው ሲመለሱ የሚሰማቸው ደስታም የአገልግሎት እርካታን እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። በአዲስ አበባ 150 የመንግሥት ተቋማት በዲጂታል ሥርዓት እየቀረቡ ሲሆን በመጀመሪያው የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎትም ስምንት ተቋማት አገልግሎት እየተሰጡ ይገኛል።
በዞኑ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተቀናጀ የድጋፍና የክትትል ሥራ እየተከናወነ ነው
May 8, 2026 41
ገንዳውኃ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተቀናጀ የድጋፍና የክትትል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው የብሔራዊና ክልላዊ ፈተናዎችን ቅድመ ዝግጅት በማስመልከት የንቅናቄ መድረክ በገንዳ ውኃ ከተማ ዛሬ አካሄዷል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ አያና በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በዞኑ የተማሪዎችን የፈተና ውጤት ለማሻሻል የተቀናጁ የድጋፍና የክትትል ሥራዎች እየተካሔዱ ይገኛል። በተለይም የ12ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተናው ብቁ እንዲሆኑ የሞዴል ፈተናና የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በመማር ማስተማሩ ከሚደረግላቸው ድጋፍ በተጨማሪም ተፈታኞቹ የስነ-ልቦና ዝግጅት ለማድረግ የሚያስችላቸው ስራ መሰራቱን አስረድተዋል። በተጨማሪም ቤተመጽሐፍቶችን ክፍት በማድረግ ተፈታኞቹ በትርፍ ጊዜያቸው እንዲያጠኑና በቡድን እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በዘንድሮው ፈተና የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻልም ትምህርት ቤቶች የአካባቢያቸውን ነባራዊ ሁኔታ መሰረት ያደረገ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙም አመላክተዋል። በገንዳውኃ ከተማ የቁጥር 2- 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርእሰ መምህር ማስረሻ መኮንን በበኩላቸው፤ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከወላጆች ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው ብለዋል። ተማሪዎች ከትምህርት ሰዓት ውጭም በትምህርት ቤቱ ተገኝተው ተጨማሪ ድጋፍ እንዲያገኙ እያደረግን ነው ብለዋል። የመተማ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር መንገሻ ብርሃን እንዳሉት፤በተያዘው ዓመት አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎችን በማስገንባት በተለይም ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ የማድረግ ስራ ተሰርቷል። የፈተና ዝግጅቱና የድጋፍ ስራው እስከ ፈተናው እለት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታውቋል።
ፖለቲካ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ማህበሩ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል
May 8, 2026 82
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን የጋምቤላ ክልል ወጣቶች ማህበር አስታወቀ። የጋምቤላ ክልል ወጣቶች ማህበር ያሉትን አደረጃጀቶች በማስተባበር ዘንድሮ ለሚካሄደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በንቃት እንዲሳተፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል። የማህበሩ ስራ አስኪያጅ ወጣት ሰለሞን አሰፋ እንደገለፀው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ መሠረት የሚጥል ነው። በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመሰረተ መንግስት ደግሞ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንደሚኖረው ጠቅሰው ይህም ለዜጎች የጋራ እድገትና ልማት መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል። ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማህበሩ ሌሎች የሲቪል ማህበራትና የወጣቶች አደረጃጀቶች ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም ህዝቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያቀርቧቸውን ፕሮግራሞችና ፖሊሲዎች በአግባቡ በመረዳት በቀጣይ ለሀገሪቱ የሚጠቅም ፓርቲ እንዲመርጡ ማህበሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ማህበሩ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉት አደረጃጀቶቹ በመጠቀም ህዝቡ ህገ-መንግስታዊ መብቱን በመጠቀም በጠቅላላ ምርጫው ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ግንዛቤ እየፈጠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተመሳሳይ የሲቪል ማህበራትም ጠቅላላ ምርጫው ነፃ፣ ፍትኃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲከናወን ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ሚናቸው የጎላ መሆኑን ወጣት ሰለሞን ገልጿል።
ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት የሴቶችና የወጣቶች አደረጃጀቶች የድርሻቸውን ይወጣሉ
May 8, 2026 65
ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 30/2018(ኢዜአ)፡-ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ አባሎቻቸው የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የሲዳማ ክልል የሴቶች እና የወጣቶች አደረጃጀቶች ገለጹ። ኢዜአ በሀዋሳ ከተማ ያነጋገራቸው የክልሉ የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶች እንደገለጹት ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ በተለያየ መንገድ ተሳትፏቸውን ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ ነው፡፡ የክልሉ ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወጣት በቃሉ መሰረት እንዳለው ወጣቱ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ ድምጹን ለፈለገው ፓርቲ እንዲሰጥና ለምርጫው ስኬታማነት የበኩሉን እንዲወጣ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በክልሉ የማህበሩ አባል የሆኑ ወጣቶች በምርጫው መሳተፍ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በወቅቱ እንዲወስዱ መደረጉን ገልጿል። የምርጫ ካርድ መውሰድ ብቻ በቂ አይደለም ያለው ወጣት በቃሉ፣ በድምጽ መስጫው እለትም ድምጻቸውን በነጻነት መስጠት እንዲችሉ የማስገንዘብ ሥራ መሰራቱን ተናግሯል። ህብረተሰቡ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ወጣቶች የመቀስቀስና የማስተማር ሥራ ከመስራቱ ባለፈ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት የበኩሉን እንዲወጣ የማስገንዘብ ስራም መከናወኑን አመልክተዋል። የክልሉ ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ገነት ማርቆስ በበኩላቸው እንዳሉት የክልሉ ሴቶች በምርጫው በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ በተሰጠው የግንዛቤ ስልጠና በርካቶች ለመራጭነት ብቁ የሚያደርጋቸውን ካርድ ወስደዋል። ከዚህ ባለፈ ፌዴሬሽኑን ወክለው በታዛቢነት የሚያገለግሉ 65 ሴቶችን በመመልመል ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ጋር በትብብር ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመዋል። ሴቶች በቤተሰብ ውስጥ ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው ያነሱት ወይዘሮ ገነት፣ ለምርጫው አሳታፊነትና ሰላማዊነት ወጣቶች የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ከቤተሰብ ጀምሮ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ የማስገንዘብ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል። የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት ጋማርሳ ዲዳ እንዳለው፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ እስከ ወረዳ ባሉ የወጣት አደረጃጀቶች በቅንጅት እየተሰራ ነው። ወጣቱ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ እንዲወስድ ተደርጓል ያለው ፕሬዚዳንቱ፣ በካርዱም ይበጀኛል የሚለውን ለመምረጥ ዝግጅት እንዲያደርግ የማስገንዘብ ሥራ መሰራቱን ተናግሯል።
ፓርቲው ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ አድርጓል
May 8, 2026 98
ጎንደር፤ ሚያዚያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጉን በጎንደር ከተማ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ገለጹ፡፡ ፓርቲው በጎንደር ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ አካሄዷል። የምርጫ ቅስቀሳውንና የድጋፍ ሰልፉን የተሳተፉ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች እንደገለፁት፤ ምርጫ ለዘላቂ ሰላም መስፈን ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ ወደፊት የሚመራቸውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በቅስቀሳው የተሳተፉት አቶ ዮሃንስ አንዱአለም እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ በለውጡ ዓመታት ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን መተግበር ችሏል።፡ ምርጫውን ሰላማዊ፣ ነጻና ተዓማኒ በማድረግ ዘላቂ እድገትን ለማረጋገጥ የመራጩ ህዝብ የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እርሳቸውም በምርጫው በንቃት እንደሚሳተፉ ገልጸዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ፅጌ ቸኮል በበኩላቸው ለሴቶች መብትና ጥቅም መረጋገጥ የሚሰራውን ፓርቲ ለመምረጥ ራሴን አዘጋጅቻለሁ ብለዋል፡፡ "ምርጫ የሰለጠነ ህዝብ የሚተገብረው የዴሞክራሲ ባህል መገለጫ ነው" ያሉት ወይዘሮ ጽጌ ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ አበራ በሪሁን በበኩላቸው ምርጫ የህዝቦች የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጫ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያን የሚያሻግር ሃሳብና ራእይ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ የተጀመሩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች እንዲቀጥሉ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ለማሳካት እንደሚሰሩም አመልክተዋል። በምረጡኝ ቅስቀሳው ስነ-ስርዓት ላይም በጎንደር ከተማ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ተሳትፈዋል።
የአፍሪካውያን አዲሱ የተፅዕኖ ድምፅ በዓላማ የሚመራ የአህጉሪቱንና የትውልዱን ተስፋና ዕድሎች የሚያሳይ መሆን አለበት
May 8, 2026 123
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ) ፦ የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ አህጉራዊ አንድነትን ለመገንባት የሚወሰድ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ ገለጹ፡፡ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ(ASMIS-2026) እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ''ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣ የአሕጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶችን ለማስመዝገብ፣ የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር የጋራ ምክክር ይደረግበታል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ፤ ጉባኤው የአህጉሪቱን የዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስን ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። የፐልስ ኦፍ አፍሪካ መወለድ መነሻ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አርቆ አሳቢ ራዕይ መሆኑን አስታውሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፍሪካ የራሷ ድምጽ እንደሚያስፈልጋትና የራሷን ታሪክ በራሷ ልጆች መተረክ እንዳለባት ባስቀመጡት መሰረት፣ ተቋሙ እውነተኛ አፍሪካዊ ትርክቶችን ለማሰራጨት በግልጽ ተልዕኮ መመስረቱን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በታላቅ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ጠቅሰው ከ30 በላይ በሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ውስጥ ተደራሽነቱን ማስፋቱንና ተቀባይነትን ማግኘቱን ጠቁመዋል። "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው ጉባኤው አህጉራዊ ተፅዕኖን ለማሳደግና ለማነቃቃት ያለመ መሆኑንም አብራርተዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተዕፅኖ ዘመኑን በዋጀ አዲስ ዕይታ ሊበየን እንደሚገባው በማንሳት፥ ለዚህም በዓላማና በኃላፊነት የሚመራ እንዲሁም ውጤት የሚያመጣ ሊሆን እንደሚገባው አፅንኦት ሰጥተዋል። የዲጂታል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የአፍሪካን ትርክት ለመቀየር ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የዲጂታል ተጽዕኖን ለማዝናናት ብቻ ሳይሆን ለማስተማር፣ አንድነትን ለማጠናከርና አህጉሪቱን ለመገንባት መጠቀም እንዳለባቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሴቶችን መሪነት የሚያጎላና ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት፣ ብዝበዛና በደል የሚቃወም የዲጂታል ተፅዕኖ መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሰው አብሮነትን፣ የትውልዱን ተስፋና ዕድሎች አጉልተው የሚያሳዩ ትርክቶችን ማስፋት እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካን ታላቅነትና ባህል በማስተዋወቅ ወጣቱን ትውልድ ለፈጠራና ለልማት ማነቃቃት እንደሚገባቸውም ጠቁመዋል፡፡ ይህንን አዲስ ንቅናቄ የሰው ዘር መገኛ፣ የአፍሪካ መዲና እና የአህጉሪቱ የጽናት ምልክት ከሆነቸው ሀገር-ኢትዮጵያ መጀመር እንደሚገባም ነው ያነሱት። ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ያላቸውን ተቀባይነት በጥበብ፣ በድፍረት እና ለአፍሪካ ባለ ጥልቅ ፍቅር መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አፍሪካውያን የራሳቸውን ታሪክ እንዲተርኩ ላደረጉት እገዛና ለአህጉሪቱ እድገት ላላቸው ቁርጠኝነት ታላቅ አክብሮታቸውን ገልጸዋል። ለጉባኤው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ለቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ለኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና ለሌሎችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የአህጉሪቱ የባህል አምባሳደርና የአዲሱ ትውልድ ድምፅ መሆን አለባቸው
May 8, 2026 99
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የአህጉሪቱ የባህል አምባሳደርና የአዲሱ ትውልድ ድምፅ መሆን እንዳለባቸው የኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገመዳ ኦላና ገለጹ። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ''ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ጉባኤ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። ጉባኤው ኃላፊነት የሚሰማቸው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማጠናከር፣ ትብብርን ለመፍጠርና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ግብን ለማሳካት ያለመ ነው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣ የአህጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶች ለማስመዝገብ እና የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር ምክክር ይደረግበታል። በጉባኤው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገለግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፣ የአፍሪካ ሕብረት ተወካዮችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገመዳ ኦላና በመድረኩ፤ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የስልጣኔ ፈር ቀዳጅ፣ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ቀንዲል የብዝሃ ቅርሶችና የቱሪስት መዳረሻ ናት ብለዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤም ስብሰባ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የዲጂታል ንቅናቄ ለመፍጠር የመጀመሪያ እንደሚሆን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የታሪክ ሃብታም፣ የፈጣን ኢኮኖሚ ዕድገት ባለቤት፣ በዲጂታል አብዮት አስደናቂ የለውጥ ምኅዋር ላይ የምትገኝ መሆኗን ተናግረዋል። የአህጉሪቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ልጆቿም የመላው አፍሪካ ታሪክ ነጋሪ፣ የባህል አምባሳደር የአዲሱ ትውልድ ድምፅ መሆን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የአህጉሪቱን ፈጠራና ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር ማገናኛ ድልድይ መሆን እንደሚጠበቅባቸውም አንስተዋል። ጉባኤው የአፍሪካ የዲጂታል እንቅስቃሴ ጅማሮ መሆኑን ጠቁመው፤ ግባችን በአፍሪካ ዓለምአቀፍ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ማፍራት ነው ብለዋል።
የክልሉ ወጣቶች ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲካሄድ እየተወጡ ያሉትን ሃላፊነት ያጠናክራሉ-ኮሚሽኑ
May 8, 2026 82
ጂንካ፤ሚያዚያ 30/2018(ኢዜአ) ፡-የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲካሄድ እየተወጡ ያሉትን ሃላፊነት አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ የክልሉ ወጣቶችና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን አመለከተ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ የወጣት ተወካዮች፣ ለወጣት አደረጃጀቶች፣ ለማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና በጂንካ ከተማ እየተሰጠ ነው። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማቲዮስ በወቅቱ እንዳመለከቱት፤ የክልሉ ወጣቶች ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲካሄድ እየተወጡ ያሉትን ሃላፊነት አጠናክረው ሊያስቀጥሉ ይገባል። በክልሉ ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ መውሰዳቸውንና ሀገራችን ወደ ዴሞክራሲያዊ ምዕራፍ ለመሸጋገር በምታደርገው ጥረት ሚናቸውን እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በክልሉ ከ2 ሺህ በላይ ወጣቶች የምርጫ ሂደቱን ለመታዘብ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና ማግኘታቸውን ጠቁመው ወጣቶች አካባቢያቸውን በንቃት በመጠበቅ ምርጫው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። በአቅም ግንባታ ስልጠናው የተሳተፉ ወጣቶችም ምርጫው ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻውን እንደሚወጡም ገልጸዋል ። የጂንካ ከተማ ነዋሪው ወጣት ሀቁ ገዛኸኝ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምንመኛትን ኢትዮጵያ ለመገንባት ወሳኝ ምዕራፍ በመሆኑ የበለፀገችውን ኢትዮጵያ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የድርሻዬን እወጣለሁ ነው ያለው። የማህበራዊ ሚዲያ አንቂው ፍቃዱ ደገፌ በበኩሉ ሀገራዊ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ወጣቱ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በምርጫው እንዲሳተፍ ግንዛቤ በመፍጠር፣ በመቀስቀስና በማስተባበር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጿል። የባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ ነዋሪ ወጣት ታምራት ደጄ በበኩሉ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶች በመራጭነት፣ በምርጫ ታዛቢነት እና በደንብ አስከባሪነት እንዲሳተፉ በማስተባበር ለምርጫው ስኬታማነት የድርሻውን እየተወጣ መሆኑንም አረጋግጧል። ወጣት አንለይ አካልቆ በበኩሏ ካርድ ከመውሰድ አንስቶ ለሴቶች ግንዛቤ በመፍጠር በምርጫው በንቃት እንዲሳተፉ የማስተባበር ስራ እየሰራች እንዳለች ገልፃለች። ግንቦት 24 በሚካሄደው ምርጫ ለሀገሪቱ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ በጉጉት እየጠበቀች መሆኑንም ጠቁማለች። በአቅም ግንባታ ስልጠናው በምርጫው የወጣቶች ሚና፣ የምርጫ ስነ-ምግባርና ህጎች ዙሪያ የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ውይይት እየተደረገ ይገኛል። በአቅም ግንባታ ስልጠናው በክልሉ ከሚገኙ ከሁሉም ዞኖች የተወጣጡ ወጣቶች፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችና የማህበረሰብ አንቂዎች ተሳትፈዋል።
በክልሉ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶች ተሳትፎን የማጎልበት ተግባራት ይጠናከራሉ-ፌዴሬሽኑ
May 8, 2026 111
ሆሳዕና ፤ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ለማጎልበት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ሴቶች ፌዴሬሽን ገለፀ። የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ፋጡማ ተሰማ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ፌዴሬሽኑ የክልሉ ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ ይቀጥላል። በክልሉ የምርጫ ሂደቱን አካታችና ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ 3 ሺህ 500 የምርጫ ታዛቢዎችን የመለየትና የማሰልጠን ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። የጎዳና ላይ ሩጫን ጨምሮ ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ማህበረሰቡ በወሰደው ካርድ ድምፅ የመስጠት መብቱን እንዲጠቀም ተገቢ ግንዛቤ እየተፈጠረ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ሴቶች በምርጫው የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የክልሉ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ፎዚያ መሀመድ በበኩላቸው፤ ማህበሩ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችል ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በክልሉ ለምርጫ ታዛቢነት የተለዩ ሴቶችን ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር የታዛቢነት መለያ እንዲሰጣቸው ተደርጓል ብለዋል። በምርጫ ሂደቱ የሴቶችን የመምረጥና የመመረጥ ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው ተግባሩ ምርጫው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል። በሆሳዕና ከተማ የሴቶች ማህበር አባል ወይዘሮ ትዕግስት ፍርዱ እንደገለፁት ፤የምርጫ ሂደቱን ተዓማኒና ፍትሀዊ ለማድረግ የሚያስችላቸውን የታዛቢነት ስልጠና ወስደዋል። የወሰዱትን ስልጠና መነሻ በማድረግ ማህበረሰቡ በወሰደው ካርድ ድምፅ የመስጠት መብቱን እንዲጠቀም የሚያስችል ግንዛቤ እየፈጠሩ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት፡፡
በምርጫው የዜጎች ተሳትፎን ለማሳደግና ሂደቱም ሠላማዊና ተአማኒ እንዲሆን የድርሻችንን እየተወጣን ነው - የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች
May 8, 2026 166
ሀዋሳ፤ሚያዚያ 30/2018(ኢዜአ):-በጠቅላላ ምርጫው የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎን ለማሳደግና ሂደቱም ሠላማዊና ተአማኒ እንዲሆን የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለፁ። በሀዋሳና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በንቃት በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ የማስገንዘብ ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሲዳማ ክልል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አስተባባሪ አቶ ማስረሻ ክብረት እንዳሉት፣ በሲዳማ ክልል ያሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ ነው። በዚህም የዜጎችን ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎን ለማሳደግ እና ሂደቱ ሠላማዊና ተአማኒ እንዲሆን ለማስቻል ዜጎችን በማንቃት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል። ድርጅቶቹ ለመራጮች ትምህርት ሲሰጡ ሕግና አዋጅን ተከትሎ ከመስራት ባለፈ ምርጫው አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል። በምርጫው ሂደት ቁልፍ ሚና ካላቸው የመንግስት አካላት ጋር በመቀናጀት የምርጫው ሂደት ሠላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ እንዲሆን ድርጅቶቹ እየሰሩ መሆኑንም አቶ ማስረሻ ገልጸዋል፡፡ የእስካሁኑ የምርጫ ሂደትም አሳታፊ፣ ፍትሃዊና ሠላማዊ መሆኑንም ተናግረዋል። የሪሰረክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን አስፈፃሚ ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም በላቸው በበኩላቸው እንዳሉት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን በሚገኙ ወረዳዎች ለመራጩ ህዝብ ትምህርት እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ከዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በምርጫ ሂደትና ተሳትፎ ላይ በቂ ሥልጠና መሰጠቱን ጠቅሰው፣ ወጣቶቹም ወደየመጡበት አካባቢ በመሄድ የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሳደግ ሥራ እየሰሩ ይገኛል ብለዋል። በተለይም በሲዳማ ባህል “ዋሬ” የተሰኘውን የማህበራዊ መስተጋብር ማጠናከሪያ መድረክ በመጠቀም የመራጮች ትምህርትና ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በእስካሁኑ ሂደትም ከ100 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ተሰርቷል ብለዋል። ሥልጠና ከወሰዱ ወጣቶች መካከል የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ ወጣት አለማየሁ አበራ ምርጫ የነገ መሪን በነጻነት ለመምረጥ የሚያስችል ዴሞክራሲያዊ ሂደት መሆኑን ተናግሯል፡፡ በስልጠና ያገኘውን ግንዛቤ ከሌሎች ወጣቶች ጋር በመሆን የተለያዩ ባህላዊ መስተጋብርን በመጠቀም ህብረተሰቡን የማስተማር ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ገልጿል። የሸበዲኖ ወረዳ ነዋሪ ወጣት ዘሪሁን ሰለሞን በበኩሉ ስለ ምርጫ ሂደት እና ስለ ምርጫ ቦርዱ አሰራር ግንዛቤ በሥልጠና ማግኘት መቻሉን ተናግሯል። ያገኘውን እውቀት ለአካባቢው ህብረተሰብ በማካፈል የምርጫ ካርድ እንዲወስዱና አንድ ድምጽ ትልቅ ዋጋ እንዳለው እንዲረዱ ማድረጉን ገልጿል።
ፖለቲካ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ማህበሩ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል
May 8, 2026 82
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን የጋምቤላ ክልል ወጣቶች ማህበር አስታወቀ። የጋምቤላ ክልል ወጣቶች ማህበር ያሉትን አደረጃጀቶች በማስተባበር ዘንድሮ ለሚካሄደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በንቃት እንዲሳተፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል። የማህበሩ ስራ አስኪያጅ ወጣት ሰለሞን አሰፋ እንደገለፀው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ መሠረት የሚጥል ነው። በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመሰረተ መንግስት ደግሞ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንደሚኖረው ጠቅሰው ይህም ለዜጎች የጋራ እድገትና ልማት መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል። ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማህበሩ ሌሎች የሲቪል ማህበራትና የወጣቶች አደረጃጀቶች ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም ህዝቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያቀርቧቸውን ፕሮግራሞችና ፖሊሲዎች በአግባቡ በመረዳት በቀጣይ ለሀገሪቱ የሚጠቅም ፓርቲ እንዲመርጡ ማህበሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ማህበሩ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉት አደረጃጀቶቹ በመጠቀም ህዝቡ ህገ-መንግስታዊ መብቱን በመጠቀም በጠቅላላ ምርጫው ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ግንዛቤ እየፈጠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተመሳሳይ የሲቪል ማህበራትም ጠቅላላ ምርጫው ነፃ፣ ፍትኃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲከናወን ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ሚናቸው የጎላ መሆኑን ወጣት ሰለሞን ገልጿል።
ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት የሴቶችና የወጣቶች አደረጃጀቶች የድርሻቸውን ይወጣሉ
May 8, 2026 65
ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 30/2018(ኢዜአ)፡-ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ አባሎቻቸው የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የሲዳማ ክልል የሴቶች እና የወጣቶች አደረጃጀቶች ገለጹ። ኢዜአ በሀዋሳ ከተማ ያነጋገራቸው የክልሉ የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶች እንደገለጹት ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ በተለያየ መንገድ ተሳትፏቸውን ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ ነው፡፡ የክልሉ ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወጣት በቃሉ መሰረት እንዳለው ወጣቱ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ ድምጹን ለፈለገው ፓርቲ እንዲሰጥና ለምርጫው ስኬታማነት የበኩሉን እንዲወጣ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በክልሉ የማህበሩ አባል የሆኑ ወጣቶች በምርጫው መሳተፍ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በወቅቱ እንዲወስዱ መደረጉን ገልጿል። የምርጫ ካርድ መውሰድ ብቻ በቂ አይደለም ያለው ወጣት በቃሉ፣ በድምጽ መስጫው እለትም ድምጻቸውን በነጻነት መስጠት እንዲችሉ የማስገንዘብ ሥራ መሰራቱን ተናግሯል። ህብረተሰቡ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ወጣቶች የመቀስቀስና የማስተማር ሥራ ከመስራቱ ባለፈ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት የበኩሉን እንዲወጣ የማስገንዘብ ስራም መከናወኑን አመልክተዋል። የክልሉ ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ገነት ማርቆስ በበኩላቸው እንዳሉት የክልሉ ሴቶች በምርጫው በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ በተሰጠው የግንዛቤ ስልጠና በርካቶች ለመራጭነት ብቁ የሚያደርጋቸውን ካርድ ወስደዋል። ከዚህ ባለፈ ፌዴሬሽኑን ወክለው በታዛቢነት የሚያገለግሉ 65 ሴቶችን በመመልመል ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ጋር በትብብር ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመዋል። ሴቶች በቤተሰብ ውስጥ ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው ያነሱት ወይዘሮ ገነት፣ ለምርጫው አሳታፊነትና ሰላማዊነት ወጣቶች የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ከቤተሰብ ጀምሮ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ የማስገንዘብ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል። የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት ጋማርሳ ዲዳ እንዳለው፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ እስከ ወረዳ ባሉ የወጣት አደረጃጀቶች በቅንጅት እየተሰራ ነው። ወጣቱ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ እንዲወስድ ተደርጓል ያለው ፕሬዚዳንቱ፣ በካርዱም ይበጀኛል የሚለውን ለመምረጥ ዝግጅት እንዲያደርግ የማስገንዘብ ሥራ መሰራቱን ተናግሯል።
ፓርቲው ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ አድርጓል
May 8, 2026 98
ጎንደር፤ ሚያዚያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጉን በጎንደር ከተማ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ገለጹ፡፡ ፓርቲው በጎንደር ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ አካሄዷል። የምርጫ ቅስቀሳውንና የድጋፍ ሰልፉን የተሳተፉ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች እንደገለፁት፤ ምርጫ ለዘላቂ ሰላም መስፈን ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ ወደፊት የሚመራቸውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በቅስቀሳው የተሳተፉት አቶ ዮሃንስ አንዱአለም እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ በለውጡ ዓመታት ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን መተግበር ችሏል።፡ ምርጫውን ሰላማዊ፣ ነጻና ተዓማኒ በማድረግ ዘላቂ እድገትን ለማረጋገጥ የመራጩ ህዝብ የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እርሳቸውም በምርጫው በንቃት እንደሚሳተፉ ገልጸዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ፅጌ ቸኮል በበኩላቸው ለሴቶች መብትና ጥቅም መረጋገጥ የሚሰራውን ፓርቲ ለመምረጥ ራሴን አዘጋጅቻለሁ ብለዋል፡፡ "ምርጫ የሰለጠነ ህዝብ የሚተገብረው የዴሞክራሲ ባህል መገለጫ ነው" ያሉት ወይዘሮ ጽጌ ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ አበራ በሪሁን በበኩላቸው ምርጫ የህዝቦች የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጫ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያን የሚያሻግር ሃሳብና ራእይ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ የተጀመሩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች እንዲቀጥሉ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ለማሳካት እንደሚሰሩም አመልክተዋል። በምረጡኝ ቅስቀሳው ስነ-ስርዓት ላይም በጎንደር ከተማ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ተሳትፈዋል።
የአፍሪካውያን አዲሱ የተፅዕኖ ድምፅ በዓላማ የሚመራ የአህጉሪቱንና የትውልዱን ተስፋና ዕድሎች የሚያሳይ መሆን አለበት
May 8, 2026 123
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ) ፦ የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ አህጉራዊ አንድነትን ለመገንባት የሚወሰድ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ ገለጹ፡፡ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ(ASMIS-2026) እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ''ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣ የአሕጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶችን ለማስመዝገብ፣ የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር የጋራ ምክክር ይደረግበታል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ፤ ጉባኤው የአህጉሪቱን የዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስን ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። የፐልስ ኦፍ አፍሪካ መወለድ መነሻ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አርቆ አሳቢ ራዕይ መሆኑን አስታውሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፍሪካ የራሷ ድምጽ እንደሚያስፈልጋትና የራሷን ታሪክ በራሷ ልጆች መተረክ እንዳለባት ባስቀመጡት መሰረት፣ ተቋሙ እውነተኛ አፍሪካዊ ትርክቶችን ለማሰራጨት በግልጽ ተልዕኮ መመስረቱን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በታላቅ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ጠቅሰው ከ30 በላይ በሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ውስጥ ተደራሽነቱን ማስፋቱንና ተቀባይነትን ማግኘቱን ጠቁመዋል። "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው ጉባኤው አህጉራዊ ተፅዕኖን ለማሳደግና ለማነቃቃት ያለመ መሆኑንም አብራርተዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተዕፅኖ ዘመኑን በዋጀ አዲስ ዕይታ ሊበየን እንደሚገባው በማንሳት፥ ለዚህም በዓላማና በኃላፊነት የሚመራ እንዲሁም ውጤት የሚያመጣ ሊሆን እንደሚገባው አፅንኦት ሰጥተዋል። የዲጂታል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የአፍሪካን ትርክት ለመቀየር ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የዲጂታል ተጽዕኖን ለማዝናናት ብቻ ሳይሆን ለማስተማር፣ አንድነትን ለማጠናከርና አህጉሪቱን ለመገንባት መጠቀም እንዳለባቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሴቶችን መሪነት የሚያጎላና ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት፣ ብዝበዛና በደል የሚቃወም የዲጂታል ተፅዕኖ መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሰው አብሮነትን፣ የትውልዱን ተስፋና ዕድሎች አጉልተው የሚያሳዩ ትርክቶችን ማስፋት እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካን ታላቅነትና ባህል በማስተዋወቅ ወጣቱን ትውልድ ለፈጠራና ለልማት ማነቃቃት እንደሚገባቸውም ጠቁመዋል፡፡ ይህንን አዲስ ንቅናቄ የሰው ዘር መገኛ፣ የአፍሪካ መዲና እና የአህጉሪቱ የጽናት ምልክት ከሆነቸው ሀገር-ኢትዮጵያ መጀመር እንደሚገባም ነው ያነሱት። ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ያላቸውን ተቀባይነት በጥበብ፣ በድፍረት እና ለአፍሪካ ባለ ጥልቅ ፍቅር መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አፍሪካውያን የራሳቸውን ታሪክ እንዲተርኩ ላደረጉት እገዛና ለአህጉሪቱ እድገት ላላቸው ቁርጠኝነት ታላቅ አክብሮታቸውን ገልጸዋል። ለጉባኤው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ለቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ለኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና ለሌሎችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የአህጉሪቱ የባህል አምባሳደርና የአዲሱ ትውልድ ድምፅ መሆን አለባቸው
May 8, 2026 99
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የአህጉሪቱ የባህል አምባሳደርና የአዲሱ ትውልድ ድምፅ መሆን እንዳለባቸው የኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገመዳ ኦላና ገለጹ። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ''ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ጉባኤ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። ጉባኤው ኃላፊነት የሚሰማቸው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማጠናከር፣ ትብብርን ለመፍጠርና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ግብን ለማሳካት ያለመ ነው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣ የአህጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶች ለማስመዝገብ እና የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር ምክክር ይደረግበታል። በጉባኤው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገለግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፣ የአፍሪካ ሕብረት ተወካዮችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገመዳ ኦላና በመድረኩ፤ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የስልጣኔ ፈር ቀዳጅ፣ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ቀንዲል የብዝሃ ቅርሶችና የቱሪስት መዳረሻ ናት ብለዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤም ስብሰባ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የዲጂታል ንቅናቄ ለመፍጠር የመጀመሪያ እንደሚሆን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የታሪክ ሃብታም፣ የፈጣን ኢኮኖሚ ዕድገት ባለቤት፣ በዲጂታል አብዮት አስደናቂ የለውጥ ምኅዋር ላይ የምትገኝ መሆኗን ተናግረዋል። የአህጉሪቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ልጆቿም የመላው አፍሪካ ታሪክ ነጋሪ፣ የባህል አምባሳደር የአዲሱ ትውልድ ድምፅ መሆን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የአህጉሪቱን ፈጠራና ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር ማገናኛ ድልድይ መሆን እንደሚጠበቅባቸውም አንስተዋል። ጉባኤው የአፍሪካ የዲጂታል እንቅስቃሴ ጅማሮ መሆኑን ጠቁመው፤ ግባችን በአፍሪካ ዓለምአቀፍ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ማፍራት ነው ብለዋል።
የክልሉ ወጣቶች ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲካሄድ እየተወጡ ያሉትን ሃላፊነት ያጠናክራሉ-ኮሚሽኑ
May 8, 2026 82
ጂንካ፤ሚያዚያ 30/2018(ኢዜአ) ፡-የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲካሄድ እየተወጡ ያሉትን ሃላፊነት አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ የክልሉ ወጣቶችና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን አመለከተ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ የወጣት ተወካዮች፣ ለወጣት አደረጃጀቶች፣ ለማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና በጂንካ ከተማ እየተሰጠ ነው። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማርቆስ ማቲዮስ በወቅቱ እንዳመለከቱት፤ የክልሉ ወጣቶች ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲካሄድ እየተወጡ ያሉትን ሃላፊነት አጠናክረው ሊያስቀጥሉ ይገባል። በክልሉ ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ መውሰዳቸውንና ሀገራችን ወደ ዴሞክራሲያዊ ምዕራፍ ለመሸጋገር በምታደርገው ጥረት ሚናቸውን እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በክልሉ ከ2 ሺህ በላይ ወጣቶች የምርጫ ሂደቱን ለመታዘብ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና ማግኘታቸውን ጠቁመው ወጣቶች አካባቢያቸውን በንቃት በመጠበቅ ምርጫው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። በአቅም ግንባታ ስልጠናው የተሳተፉ ወጣቶችም ምርጫው ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻውን እንደሚወጡም ገልጸዋል ። የጂንካ ከተማ ነዋሪው ወጣት ሀቁ ገዛኸኝ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምንመኛትን ኢትዮጵያ ለመገንባት ወሳኝ ምዕራፍ በመሆኑ የበለፀገችውን ኢትዮጵያ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የድርሻዬን እወጣለሁ ነው ያለው። የማህበራዊ ሚዲያ አንቂው ፍቃዱ ደገፌ በበኩሉ ሀገራዊ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ወጣቱ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በምርጫው እንዲሳተፍ ግንዛቤ በመፍጠር፣ በመቀስቀስና በማስተባበር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጿል። የባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ ነዋሪ ወጣት ታምራት ደጄ በበኩሉ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶች በመራጭነት፣ በምርጫ ታዛቢነት እና በደንብ አስከባሪነት እንዲሳተፉ በማስተባበር ለምርጫው ስኬታማነት የድርሻውን እየተወጣ መሆኑንም አረጋግጧል። ወጣት አንለይ አካልቆ በበኩሏ ካርድ ከመውሰድ አንስቶ ለሴቶች ግንዛቤ በመፍጠር በምርጫው በንቃት እንዲሳተፉ የማስተባበር ስራ እየሰራች እንዳለች ገልፃለች። ግንቦት 24 በሚካሄደው ምርጫ ለሀገሪቱ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ በጉጉት እየጠበቀች መሆኑንም ጠቁማለች። በአቅም ግንባታ ስልጠናው በምርጫው የወጣቶች ሚና፣ የምርጫ ስነ-ምግባርና ህጎች ዙሪያ የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ውይይት እየተደረገ ይገኛል። በአቅም ግንባታ ስልጠናው በክልሉ ከሚገኙ ከሁሉም ዞኖች የተወጣጡ ወጣቶች፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችና የማህበረሰብ አንቂዎች ተሳትፈዋል።
በክልሉ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶች ተሳትፎን የማጎልበት ተግባራት ይጠናከራሉ-ፌዴሬሽኑ
May 8, 2026 111
ሆሳዕና ፤ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ለማጎልበት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ሴቶች ፌዴሬሽን ገለፀ። የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ፋጡማ ተሰማ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ፌዴሬሽኑ የክልሉ ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ ይቀጥላል። በክልሉ የምርጫ ሂደቱን አካታችና ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ 3 ሺህ 500 የምርጫ ታዛቢዎችን የመለየትና የማሰልጠን ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። የጎዳና ላይ ሩጫን ጨምሮ ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ማህበረሰቡ በወሰደው ካርድ ድምፅ የመስጠት መብቱን እንዲጠቀም ተገቢ ግንዛቤ እየተፈጠረ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ሴቶች በምርጫው የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የክልሉ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ፎዚያ መሀመድ በበኩላቸው፤ ማህበሩ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችል ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በክልሉ ለምርጫ ታዛቢነት የተለዩ ሴቶችን ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር የታዛቢነት መለያ እንዲሰጣቸው ተደርጓል ብለዋል። በምርጫ ሂደቱ የሴቶችን የመምረጥና የመመረጥ ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው ተግባሩ ምርጫው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል። በሆሳዕና ከተማ የሴቶች ማህበር አባል ወይዘሮ ትዕግስት ፍርዱ እንደገለፁት ፤የምርጫ ሂደቱን ተዓማኒና ፍትሀዊ ለማድረግ የሚያስችላቸውን የታዛቢነት ስልጠና ወስደዋል። የወሰዱትን ስልጠና መነሻ በማድረግ ማህበረሰቡ በወሰደው ካርድ ድምፅ የመስጠት መብቱን እንዲጠቀም የሚያስችል ግንዛቤ እየፈጠሩ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት፡፡
በምርጫው የዜጎች ተሳትፎን ለማሳደግና ሂደቱም ሠላማዊና ተአማኒ እንዲሆን የድርሻችንን እየተወጣን ነው - የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች
May 8, 2026 166
ሀዋሳ፤ሚያዚያ 30/2018(ኢዜአ):-በጠቅላላ ምርጫው የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎን ለማሳደግና ሂደቱም ሠላማዊና ተአማኒ እንዲሆን የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለፁ። በሀዋሳና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በንቃት በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ የማስገንዘብ ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሲዳማ ክልል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አስተባባሪ አቶ ማስረሻ ክብረት እንዳሉት፣ በሲዳማ ክልል ያሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ ነው። በዚህም የዜጎችን ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎን ለማሳደግ እና ሂደቱ ሠላማዊና ተአማኒ እንዲሆን ለማስቻል ዜጎችን በማንቃት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል። ድርጅቶቹ ለመራጮች ትምህርት ሲሰጡ ሕግና አዋጅን ተከትሎ ከመስራት ባለፈ ምርጫው አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል። በምርጫው ሂደት ቁልፍ ሚና ካላቸው የመንግስት አካላት ጋር በመቀናጀት የምርጫው ሂደት ሠላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ እንዲሆን ድርጅቶቹ እየሰሩ መሆኑንም አቶ ማስረሻ ገልጸዋል፡፡ የእስካሁኑ የምርጫ ሂደትም አሳታፊ፣ ፍትሃዊና ሠላማዊ መሆኑንም ተናግረዋል። የሪሰረክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን አስፈፃሚ ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም በላቸው በበኩላቸው እንዳሉት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን በሚገኙ ወረዳዎች ለመራጩ ህዝብ ትምህርት እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ከዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በምርጫ ሂደትና ተሳትፎ ላይ በቂ ሥልጠና መሰጠቱን ጠቅሰው፣ ወጣቶቹም ወደየመጡበት አካባቢ በመሄድ የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሳደግ ሥራ እየሰሩ ይገኛል ብለዋል። በተለይም በሲዳማ ባህል “ዋሬ” የተሰኘውን የማህበራዊ መስተጋብር ማጠናከሪያ መድረክ በመጠቀም የመራጮች ትምህርትና ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በእስካሁኑ ሂደትም ከ100 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ተሰርቷል ብለዋል። ሥልጠና ከወሰዱ ወጣቶች መካከል የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ ወጣት አለማየሁ አበራ ምርጫ የነገ መሪን በነጻነት ለመምረጥ የሚያስችል ዴሞክራሲያዊ ሂደት መሆኑን ተናግሯል፡፡ በስልጠና ያገኘውን ግንዛቤ ከሌሎች ወጣቶች ጋር በመሆን የተለያዩ ባህላዊ መስተጋብርን በመጠቀም ህብረተሰቡን የማስተማር ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ገልጿል። የሸበዲኖ ወረዳ ነዋሪ ወጣት ዘሪሁን ሰለሞን በበኩሉ ስለ ምርጫ ሂደት እና ስለ ምርጫ ቦርዱ አሰራር ግንዛቤ በሥልጠና ማግኘት መቻሉን ተናግሯል። ያገኘውን እውቀት ለአካባቢው ህብረተሰብ በማካፈል የምርጫ ካርድ እንዲወስዱና አንድ ድምጽ ትልቅ ዋጋ እንዳለው እንዲረዱ ማድረጉን ገልጿል።
ማህበራዊ
የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ሚና ወሳኝ ነው
May 8, 2026 27
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና የአህጉሪቱን ትርክት በባለቤትነት ለመምራት የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ሚና ወሳኝ መሆኑን የፓናል ውይይት ተሳታፊዎች ገለጹ። በፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ሚዲያ እና በኤ.ጂ.ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ትብብር የተዘጋጀው የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና በድምሩ 321 ሚሊየን ተከታዮች ያሏቸው 61 ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 120 ኢትዮጵያውያን የይዘት ፈጣሪዎች አዲስ የዲጂታል ታሪክ ለመጻፍ በጉባኤው ታድመዋል። በጉባኤው ላይ "የአፍሪካን አዎንታዊ ገጽታ መገንባት" በሚል ርዕስ በተካሄደው የፓናል ውይይት፤ ታዋቂው ጋናዊ የይዘት ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር (ዎዴ ማያ) "ታሪካችንን እንዲነግሩልን ሌላ አካል መጠበቅ የለብንም" ሲል ተናግሯል። ትኩረቱን ዘወትር በአዎንታዊ ታሪኮች ላይ በማድረግ የአፍሪካን ውበት ለዓለም እያስተዋወቀ እንደሚገኝ የገለጸው ዎዴ ማያ፣ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ለውጦችን በራሱ ተነሳሽነት በቪዲዮ መዘገቡንና ስራዎቹም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘታቸውን አስታውቋል። የአፍሪካ መንግስታት ለሀገር በቀል ይዘት ፈጣሪዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አሳስቧል። የ2025 የዓለም ቆንጆ (Miss World Africa) ሀሴት ደረጀ በበኩሏ፤ አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ መድረኮች የራሳቸውን ማንነትና እሴት ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው ገልጻለች። ትክክለኛ ተፅዕኖ መፍጠር የሚቻለው የራስን ባህል፣ ቋንቋ እና እሴት ሳይሸራርፉ ለዓለም ማቅረብ ሲቻል መሆኑንም አስገንዝባለች። ከቱሪዝም ሚኒስቴር የመጡት አቶ ቴዎድሮስ ደርበው በበኩላቸው፤ መንግስት የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ቁልፍ አጋር ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የባህል መዳረሻ ብቻ ሳትሆን የወደፊት ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን ማሳየት እንደሚገባ ገልጸዋል፡ አፍሪካን በተመለከተ ሲነገሩ የነበሩ የተሳሳቱ ትርክቶችን ወደ ዕድገትና ፈጠራ ትርክት መቀየር እንደሚገባም በአጽንኦት ገልጸዋል።
ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል የዘመኑ ብሔራዊ አርበኝነት ነው
May 8, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል የዘመኑ ብሔራዊ አርበኝነት መሆኑን የአዲስ መሶብ ዲጂታል አንድ ማዕከል አገልግሎት ሠራተኞች ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የመጀመሪያውን የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት ማስጀመራቸው ይታወቃል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት በአፍሪካ ፈር ቀዳጅ ሥራ መሆኑን ገልጸዋል። ማንኛውም ሰው በመሶብ የአንድ ማዕከል ሲገለገል ለኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥ ዕድገት ምስክርነት የሚሰጥና ብልፅግናን የሚያረጋግጥ የአርበኝት ዘመን መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል። የመጀመሪያው የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎትም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የአዲስ አበባ የከተማዋ ክፍሎች በመዘዋወር ለዜጎች ቀልጣፋና ስሉጥ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት ሰጪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዜጎች የሚገባቸውን የመንግሥት አገልግሎት ግልፅና ቀልጣፋ ማድረግ ዘመኑ የሚጠይቀው አርበኝነት ነው። ከአገልግሎት ሰጪዎቹ መካከል ዘውዱ አምሳሉ፤ ወቅቱ የሚጠይቀው የዘመኑ አርበኝነት ህዝብን በቅንነት፣ በታማንነትና ታታሪነት ማገልገል መሆኑን ገልጸዋል። የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎቱም ዜጎች በመንግሥት አገልግሎት የሚገጥማቸውን መጉላላት በማስቀረት ቅርብና ጊዜ ቆጣቢ አገልግሎት የሚያስገኝ መሆኑን ተናግረዋል። በመጀመሪያው የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸው ታላቅ ኩራትና ደስታ የሚቸር የአርበኝነት መገለጫ መሆኑን አንስተዋል። የሚሰጡት ቀልጣፋና ግልፅ አገልግሎትም የህዝብና መንግሥትን መተማመን በማጠናከር ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንዳለው አስረድተዋል። ለመዲናዋ ነዋሪዎች የተሳለጠ አገልግሎት በማቅረብ ለመጭው ትውልድ አርዓያ የሚሆን አሻራ እያሳረፉ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ሌላኛው አገልግሎት ሰጪ ኤፍሬም አሰፋ በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ተገልጋዮች የተለያዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ስር የሚያገኙበትን ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። በዘመኑ የልማት አርበኝነት ጉዞም በተሰማሩበት ሙያ ዜጎች የሚፈልጉትን የመንግሥት አገልግሎት በግልፅና ቀልጣፋ አሰራር እየሰጡ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለመዲናዋ ነዋሪዎች የሚሰጡት የተሳለጠ ሙያዊ የመንግሥት ተቋማት አገልግሎትም እንግልትን በማስቀረት እርካታን የሚሰጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ መሶብ ተንቀሳቃሽ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመጀመሪያ ዙር ሠራተኛ በመሆኔ እጅግ ደስታ ይሰማኛል ያሉት ደግሞ የማዕከሉ አገልግሎት ሰጪ ጫልቱ ታደሰ ናቸው። ተገልጋዮች ተገልግለው ሲመለሱ የሚሰማቸው ደስታም የአገልግሎት እርካታን እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። በአዲስ አበባ 150 የመንግሥት ተቋማት በዲጂታል ሥርዓት እየቀረቡ ሲሆን በመጀመሪያው የመሶብ አንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎትም ስምንት ተቋማት አገልግሎት እየተሰጡ ይገኛል።
በዞኑ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተቀናጀ የድጋፍና የክትትል ሥራ እየተከናወነ ነው
May 8, 2026 41
ገንዳውኃ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተቀናጀ የድጋፍና የክትትል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው የብሔራዊና ክልላዊ ፈተናዎችን ቅድመ ዝግጅት በማስመልከት የንቅናቄ መድረክ በገንዳ ውኃ ከተማ ዛሬ አካሄዷል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ አያና በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በዞኑ የተማሪዎችን የፈተና ውጤት ለማሻሻል የተቀናጁ የድጋፍና የክትትል ሥራዎች እየተካሔዱ ይገኛል። በተለይም የ12ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተናው ብቁ እንዲሆኑ የሞዴል ፈተናና የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በመማር ማስተማሩ ከሚደረግላቸው ድጋፍ በተጨማሪም ተፈታኞቹ የስነ-ልቦና ዝግጅት ለማድረግ የሚያስችላቸው ስራ መሰራቱን አስረድተዋል። በተጨማሪም ቤተመጽሐፍቶችን ክፍት በማድረግ ተፈታኞቹ በትርፍ ጊዜያቸው እንዲያጠኑና በቡድን እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በዘንድሮው ፈተና የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻልም ትምህርት ቤቶች የአካባቢያቸውን ነባራዊ ሁኔታ መሰረት ያደረገ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙም አመላክተዋል። በገንዳውኃ ከተማ የቁጥር 2- 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርእሰ መምህር ማስረሻ መኮንን በበኩላቸው፤ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከወላጆች ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው ብለዋል። ተማሪዎች ከትምህርት ሰዓት ውጭም በትምህርት ቤቱ ተገኝተው ተጨማሪ ድጋፍ እንዲያገኙ እያደረግን ነው ብለዋል። የመተማ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር መንገሻ ብርሃን እንዳሉት፤በተያዘው ዓመት አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎችን በማስገንባት በተለይም ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ የማድረግ ስራ ተሰርቷል። የፈተና ዝግጅቱና የድጋፍ ስራው እስከ ፈተናው እለት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታውቋል።
በጋምቤላ ክልል የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) በሽታ መከላከያ ክትባት በዘመቻ መሰጠት ተጀመረ
May 8, 2026 144
ጋምቤላ/አሶሳ ፤ሚያዝያ 30 /2018/ (ኢዜአ) ፡- በጋምቤላ ክልል የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) በሽታ መከላከያ ክትባት ዛሬ በዘመቻ መስጠት መጀመሩን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው ለክትባት ዘመቻው ስኬታማነት የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና መላው ማህበረሰብ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም ጥሪ አቅርቧል። የቢሮው ኃላፊ ዶክተር አቤል አሰፋ በክትባት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ ሁሉም ወረዳዎችና የስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎች ከዛሬ ሚያዘያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የበሽታው መከላከያ ክትባት ቤት ለቤት በዘመቻ መሰጠት ተጀምሯል። በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በሚሰጠው ክትባትም እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑና ከ196 ሺህ ለሚበልቁ ህፃናት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ክትባቱን መስጠት ያስፈለገው በተጎራባች ሀገራት ድንበር አካባቢ የበሽታው ምልክት በመታየቱ መሆኑንም ገልጸዋል። ክትባቱንም የክልሉ ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና ከሌሎች የዘርፉ አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት መሆኑን አስረድተዋል። በክልሉ ለአራት ቀናት በሚቆየው በዚሁ የክትባት ዘመቻ ከ1 ሺህ 300 በላይ የጤና ባለሙያዎችና በጎ ፈቃደኞች መሰማራታቸውንም አክለዋል። በክልሉ ለተጀመረው የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ስኬታማነት የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና መላው የክልሉ ማህበረሰብ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉም ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል። በክትባት ማስጀመሪያ መረሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የአጋር አካላት ተወካዮች ተገኝተዋል። በተመሳሳይም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት መሰጠት ተጀምሯል። የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አብዱልሙኒየም አልበሽር በወቅቱ እንዳስታወቁት፤ የፖሊዮ በሽታ በአጎራባች ሀገር ሱዳን መከሰቱን ተከትሎ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሽታው እንዳይዛመት የቅድመ መከላከል ስራ እየተከናወነ ነው። በክትባት ዘመቻውም ከ220ሺ በላይ ህፃናት ክትባቱን እንዲወስዱ ለማድረግ ከትምህርት ቤቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ክትባቱ ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት በሁሉም የክልሉ ወረዳዎች እና የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች ቤት ለቤት እንደሚሰጥ ጠቁመው ህብረተሰቡ ህፃናትን በማስከትብ ኃላፊነቱን እንዲወጣም ጠይቀዋል፡፡ ክትባቱ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት እንደሚሰጥም ታውቋል።
ኢኮኖሚ
የህዝብን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች የተሰጠው ትኩረት ተጠናክሮ ይቀጥላል
May 8, 2026 49
ጅማ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች ግንባታ የተሰጠው ትኩረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ነመራ ቡሊ ገለጹ። በጅማ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል። በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ነመራ ቡሊ፤ በክልሉ ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት ግብ ተጥሎ እየተሰራ ነው። ለዚህም የህዝብን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል። ባለፉት ጥቂት አመታት ሰፊ የስራ ዕድልን በመፍጠር የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰራው ስራ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት መሆኑን ጠቅሰዋል። በጅማ ከተማ የተመረቁት ፕሮጀክቶችም የዚሁ አካል ናቸው ብለዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሀ ቀመር በበኩላቸው፤ የብልፅግና ጉዟችንን እያረጋገጥን እንቀጥላለን ብለዋል። ከለውጡ በኋላ እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶች ብዛት ብቻ ሳይሆን ጥራት እና ፍጥነትንም ያማከሉ ናቸው ያሉት አቶ ጠሀ የያዝናቸውን ኢኒሼቲቮች ለማሳካት ሁሌም በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። በከተማው በዚህ አመት ከ12 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑን አመልክተዋል። በከተማው በዛሬው እለት የማምረቻ ሼዶች ፣ የዶሮ እርባታ እና የገበያ ማዕከል እንዲሁም የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ተመርቋል።
በክልሉ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች የሀገር ውስጥና የውጭ ገበያ ትስስር ለመፍጠር ትኩረት ተደርጓል
May 8, 2026 73
ባህርዳር፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ተደራጅተው በማምረት ላይ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ገበያ ትስስር በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ። በቢሮው የገበያ ልማትና ግብይት ዳይሬክተር ፍቅረማርያም የኔአባት እንደገለጹት ቢሮው ወጣቶችን በማደራጀት ወደ ስራ በማስገባትና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። በዚህም ተደራጅተው በማምረት ላይ ለሚገኙ 35ሺህ 287 ኢንተርፕራይዞች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የገበያ ትስስር በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። በተፈጠረው የገበያ ትስስርም ከ7 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ግብይት መፈጸሙን ጠቁመው ትስስሩ የተፈጠረው ከተቋማት፣ ከኩባንያዎች፣ ከኢንተርፕራይዝ ለኢንተርፕራይዝና ከሌሎች ጋር ነው ብለዋል። በሀገር ውስጥ የተፈጠረው ትስስር በኮንስትራክሽን፣ በከተማ ግብርና፣ በማምረቻውና በአገልግሎት ዘርፎች ሲሆን በውጭ ሀገራት ደግሞ ኦፓል፣ ወርቅ፣ የባህላዊ አልባሳት፣ የባልትና ውጤቶችና ሌሎች ምርቶችን በመላክ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቀሪ ወራትም የተጀመረውን የገበያ ትስስር በማጠናከር አዳዲስ ለገበያ የሚሆኑ ሀገራትን በማፈላለግ የኢንተርፕራይዞችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በደሴ ከተማ ያሬድና ጓደኞቹ ሚስማር ማምረትና ማከፋፋል ማህበር አስተባባሪ ወጣት ሰለሞን ሞላ እንደገለጸው ሚስማር በማምረት ስራ ተደራጅተው ወደ ስራ በመግባት ተጠቃሚ መሆን ችለዋል። ምርታቸውንም በተመቻቸላቸው የገበያ ትስስር በደሴ ከተማና አካባቢው በማከፋፈል የተሻለ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ተናግሯል። በ2017 በጀት ዓመት ለ40ሺህ 117 ኢንተርፕራይዞች ከ7 ነጥብ 5 ቢሊየን በላይ ዋጋ ያላቸው የተለያዩ ምርቶች በውጭና በሀገር ውስጥ ገበያ ትስስር መፍጠር መቻሉንም ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በዞኑ በመጪው ክረምት የሚተከሉ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ተዘጋጅተዋል
May 8, 2026 79
ጭሮ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ከ37 ሚሊዮን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ፅህፈት ቤት ገለፀ። በጽህፈት ቤቱ የቡና እና ቅመማ ቅመም ልማት አስተባባሪ አቶ ኦሉማ በዳኔ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በመጪው ክረምት በዞኑ 13 ወረዳዎች የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል። የቡና ዝርያዎቹ አብዛኛውን ከመቻራ ግብርና ምርምር ማዕከል የተለቀቁ እና በሽታንና ድርቅን በመቋቋም በሄክታር እስከ 17 ኩንታል ምርት የመስጠት አቅም ያላቸው መሆናቸውን ነው የተናገሩት። በዞኑ የቡና ልማትን ለማስፋፋት እየተሰራ ሲሆን የአካባቢው አርሶ አደሮችም በክረምቱ ወቅት ለሚካሄደው የችግኝ ተከላ ጉድጓዶችን ማዘጋጀታቸውን አብራርተዋል። በዞኑ እስካሁን ከ129 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ተክል መሸፈኑን አመልክተው በዘንድሮው ዓመት ለተከላ የተዘጋጀው የቡና ችግኝም ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ8 ሚሊዮን ብልጫ እንዳለው አስታውቀዋል። በሚካሄደው የቡና ልማት ስራ ከ232 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆናቸውን አብራርተዋል። የቦኬ ወረዳ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ፅህፈት ቤት የቡናና ቅመማ ቅመም ልማት አስተባባሪ አቶ ኢብራሂም ሐሰን በበኩላቸው በወረዳው በዚህ ዓመት 3 ሺህ ሄክታር አዲስ መሬት በቡና ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ከቡና ዝርያዎቹ መካከል ቡልቱም የተሰኘውና ከመቻራ ግብርና ምርምር ማእከል የወጣው የቡና ችግኝ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። በቦኬ ወረዳ ቦኬ ጥቃ ቀበሌ አርሶ አደር አይሻ መሐመድ እንዳሉት ለቡና ችግኝ ጥበቃና እንክብካቤ በማድረግ የስራ ዕድል በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል። ከዚህ ባለፈም የጫት ምርት ያመርቱበት የነበረውን ሁለት ጥማድ መሬት የቡና ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ነው የገለጹት ። ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በቡና ልማት በመሳተፍ ተጠቃሚ ለመሆን መቻላቸውን የተናገሩት ደግሞ የቀበሌው አርሶ አደር ሞሚና ኢብራሂም ናቸው። በመጪው ክረምትም ከ500 በላይ ተጨማሪ የቡና ችግኞችን ለመትከል ጉድጓዶችን ማዘጋጀታቸውን ነው የተናገሩት።
የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን አሳድጎታል
May 8, 2026 125
አርባ ምንጭ ፤ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ) ፡-የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን በማሳደግ ትርጉም ባለው መልኩ ህይወታችንን ቀይሮታል ሲሉ በጋሞ ዞን የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች ገለጹ፡፡ የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች ለኢዜአ እንደገለፁት፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አመጋገባቸውን ከመቀየሩ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን አልቆታል። በዚህም መርሃ ግብሩ ህይወታቸውን ትርጉም ባለው መንገድ እንደቀየረም ተሳታፊዎቹ አፅንኦት ሰጥተዋል። በዞኑ በምዕራብ አባያ ወረዳ አንኮበር ቀበሌ "የጦይሎ ንብ አንቢዎች ማህበር ሰብሳቢ ደሰ ኡታሎ፤ የማህበሩ አባላት በንብ ማነብ ስራ ላይ በመሰማራት ከማር ሽያጭ ጥሪት እንዲያፈሩ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። አባላቱ በሚያገኙት ገቢ ከመኖሪያ ቤት ግንባታ ጀምሮ የቤት ቁሳቁሶችን በማሟላትና ልጆቻቸውን በማስተማር ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጡ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት። መንግስት ባመቻቸላቸው 19 ሄክታር ደን ውስጥ የንብ ማነብ ተግባራትን ከማከናወን ጎን ለጎን የደን ጥበቃ ስራ እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ማህበሩ በ102 ዘመናዊና በ2 ሺህ 530 ባህላዊ ቀፎዎች ማር በማምረት በየዓመቱ ከ100 ሺህ ብር በላይ እየቆጠቡ ይገኛሉ። በቦረዳ ወረዳ መሳ ቡንታዛ ቀበሌ የአንድነት የዶሮ አርቢ ማህበር ሰብሳቢ ወጣት መስፍን ደነቀ በበኩላቸው፤ በመርሃ ግብሩ ያረቧቸውን ዶሮዎች ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። መርሃ ግብሩ የወረዳው ነዋሪዎች የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ እያገዘ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቦረዳ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ደጉ ማጃ ናቸው። መርሃ ግብሩ በህብረተሰቡ መካከል መልካም የሆነ መነቃቃትና የስራ ባህልን በመፍጠር ከድህነት እንዲላቀቁ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል። የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ወርቅነህ ካልሳ በበኩላቸው፤ የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ በዞኑ በ14 ወረዳዎችና በ6 ከተማ አስተዳደሮች እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በሁሉም መዋቅሮች የወተት፣ የስጋ፣ የዶሮ፣ የማር እና የዓሣ መንደሮች የተደራጁ ሲሆን በዝርያ ማሻሻልና በጤና አገልግሎት የተቀናጀ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የአፍሪካን እውነት ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል
May 8, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን እውነት ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች ገለጹ። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛል። ጉባኤውም ኃላፊነት የሚሰማቸው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማጠናከር፣ ትብብርን ለመፍጠርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ግብን ለማሳካት ያለመ ነው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣የአህጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶችን ለማስመዝገብና የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር የጋራ ምክክር ያደርጋሉ። በጉባኤው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፣ የኤ.ጂ.ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገመዳ ኦላና፣ የአፍሪካ ህብረት ተወካዮችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። በጉባኤው ላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ዝግጅቶች ላይ ያለውን አስተዋጽኦ የሚዳስስ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የናቹራል ላንጉዌጅ ፕሮሰሲንግ ምርምር ዲቪዥን ዳይሬክተር ሳሙኤል ራህመቶ፤ ቀደም ሲል የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለባለሙያዎች የቴክኒክና የምርምር ሥራ ይውል እንደነበር ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ የማህበረሰቡን የዕለት ተእለት የሥራ እንቅስቃሴ ቀለል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣን ዕድገትም ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ የፕሮዳክሽን ሥራዎችን የሚያከናውን ምኅዳር በመፍጠር እንደ ሲኒማ የሚታዩ ምስሎችን መፍጠር እያስቻለ መሆኑን አንስተዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምስልና ድምፅ የማመንጨት አቅም ዕድገት የይዘት ፈጣሪዎችን ሥራ እያገዘ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለይዘት ዝግጅት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለአህጉሪቱ ትርክትና ገፅታ ግንባታ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአህጉሪቱን እውነተኛ ባህልና ታሪክ ለዓለም ማህበረሰብ ለመተረክም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። ሌላኛው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ብራያን ጆታ በበኩሉ፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጠራን በማላቅ የዲጂታል ክህሎትን የሚያበለፅግ የቴክኖሎጂ አማራጭ መሆኑን ገልጿል። በዚህም የአፍሪካን እውነተኛ ገፅታ ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የዲጂታል አማራጭ ክህሎትን በማሳደግ መጠቀም እንደሚያስፈልግ ተናግሯል። ቦትስዋናዊው ታዋቂ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪ ዊሊያምላስት ኬ.አር.ኤም፤ የይዘት ፈጠራ ሥራዎችን ከገንዘብ ማግኛና ቁጥር ባሻገር ለአህጉሪቱ ትርክት ግንባታ መጠቀም አለብን ብሏል። ለዚህም የሥራ ፍቅር ባህልን በማዳበር የዲጂታል አማራጮችን የአፍሪካን የተሻለ ገፅታና ትርክት በሚያጎላ መልኩ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጿል።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የሚዲያ ምህዳሩን በዲሞክራሲያዊ አውድ ለመዋጀት በወሰድነው እርምጃ ለሀገር ግንባታ የሚረዳ መሠረት ጥሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
May 7, 2026 209
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት ስምንት ዓመታት የሚዲያ ምህዳሩን በዲሞክራሲያዊ አውድ ለመዋጀት በወሰድነው እርምጃ ለሀገር ግንባታ የሚረዳ መሠረት ጥሏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ''የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ'' በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀውና ባለፉት ዓመታት በሚዲያ ዘርፍና ተቋማት ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች በቀረቡበት የምክክር መድረክ ላይ ታድሜ ሀሳቤን አጋርቻለሁ ብለዋል። ይህ ውጤት እንዲቀጥልም ሚዲያዎች ከዋልታ ረገጥነትና ከጽንፈኝነት ወጥተው በእውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት በመገንባት፣ ለጋራ ማንነትና ለብሔራዊ መግባባት በቁርጠኝነት ሊሠሩ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። ሚዲያዎቻችን በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና በጥናት የታገዘ ጥልቅ ትንተና በማቅረብ፣ ከአርዕስት ሽያጭ ባለፈ ለሀገር አጀንዳዎች ትኩረት መስጠት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ተግባራቸውም በዓላማ፣ በእይታ፣ በሙያዊ ብቃትና ለህዝብ ቅርብ በመሆን ላይ ተመስርቶ፣ ሚዛናዊነትን በጠበቀ መልኩ ለሀገር ብልጽግና መንገድ ጠራጊና ችግር ፈቺ ሆነው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል በመልዕክታቸው።
ለውጡ ትኩረቱን በእሳቤ፣ በህግና አሰራር ላይ በማድረጉ ተቋማዊ ብቃቱ እንዲያድግ አስችሎታል
May 7, 2026 124
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 29/2018 (ኢዜአ)፦ ለውጡ ትኩረቱን በእሳቤ፣ በህግና አሰራር ላይ በማድረጉ ተቋማዊ ብቃቱ እንዲያድግ ማስቻሉን የኤንቢሲ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ብሩክ ከበደ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ሐሳብ ሀገራዊ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው። የናሽናል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ብሩክ ከበደ ''የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ'' በተሰኘው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ በዘርፉ በተለይም በኤንቢሲ ጣቢያ የተመዘገቡትን የለውጡን ስኬቶች አንስተዋል። ለውጡ ትኩረቱን በዋነኛነት በእሳቤ፣ በህግና አሰራር ላይ በማድረግ፤ ተቋማዊ ብቃትና ሥነ ምግባርን ማጎልበት ማስቻሉን ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል። በተጨማሪም ለዲጂታላይዜሽን ቅድሚያ በመስጠት፣ የመረጃ ንፉግነትን ባህል በመቀየርና የወል ትርክት በመገንባት ተቀዳሚ የሚዲያ ተቋም መሆን መቻሉን አቶ ብሩክ በመድረኩ ላይ አመልክተዋል።
የሪፎርም ስራው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ብቁ፣ ተወዳዳሪና ሙያዊ ነጻነቱ የተከበረ እንዲሆን አድርጓል
May 7, 2026 114
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግስት ሪፎርም ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽንን ብቁ፣ ተወዳዳሪና ሙያዊ ነጻነቱ የተከበረ ማድረግ ማስቻሉን የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ አድማሱ ዳምጠው ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ሐሳብ ሀገራዊ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው። የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አድማሱ ዳምጠው ''የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ'' በተሰኘው የዘርፉ የምክክር መድረክ ላይ በሚዲያው ዘርፍ የለውጡ መንግስት ያስመዘገባቸው ስኬቶችን ለተቋሙ ያለውን አበርክቶ በጥልቀት አቅርበዋል። ተቋሙ ሰፊውን ሪፎርም በመቀላቀል ብቁ፣ ተወዳዳሪና ሙያዊ ነጻነቱ የተከበረ ማድረግ መቻሉን ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልጸዋል። በተጨማሪም በይዘት፣ በተለወጠ አደረጃጀት እና በቴክኖሎጂ አማራጮች ተደራሽ በመሆን ተወዳዳሪነቱን ማስፋቱን የጠቀሱት አቶ አድማሱ፤ ተቋሙ ከሪፎርሙ በመቋደሱ ከራሱ አልፎ ሰፊ የብሮድካስት ልምዱን በማካፈል ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በመጨረሻም ፈጠራን፣ የሀሳብ ብዝሀነትና አለም አቀፋዊነትን በማስፋት ተመራጭና ወቅታዊ የመረጃ ምንጭ በመሆን እያገለገለ እንደሚገኝ ዋና ስራ አስፈፃሚው አብራርተዋል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል
May 8, 2026 103
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ25ኛ ሳምንት መርሐ ግብር የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይደረጋሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ መቻል ከአዲስ አበባ ከተማ ይጫወታሉ። መቻል በ54 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው አዲስ አበባ ከተማ በ12 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ያሸነፈው መቻል በድል ጉዞ ለመቀጠል ወደ ሜዳ ይገባል። በሊጉ በርካታ ግቦች (50) ያስተናገደው አዲስ አበባ ከተማ ከተሸነፈ ወደ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ይወርዳል። በሌላኛው መርሐ ግብር ልደታ ክፍለ ከተማ ከባህር ዳር ከተማ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ልደታ ክፍለ ከተማ በ19 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ባህር ዳር ከተማ በተመሳሳይ 19 ነጥብ በግብ ክፍያ በልጦ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ድል ያልቀናው ልደታ ክፍለ ከተማ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይፋለማል። በ24ኛ ሳምንት በመቻል 3 ለ 2 የተሸነፈው ባህር ዳር ከተማ ወደ ድል መንገድ ለመመለስ ይጫወታል። ሲዳማ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ሲዳማ ቡና በ34 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ወደ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ መውረዱ የተረጋገጠው አርባምንጭ ከተማ በ10 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። በ24ኛ ሳምንት ልደታ ክፍለ ከተማን 2 ለ 0 ያሸነፈው ሲዳማ ቡና በድል ጉዞው ለመቀጠል ይጫወታል። ከፕሪሚየር ሊጉ ለወረደው አርባምንጭ ከተማ ጨዋታው ከመርሐ ግብር ማመሟያነት የዘለለ ትርጉም የለውም። የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት እስከ ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ63 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በተመሳሳይ 63 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። የኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰሎሞን በ24 ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራች ይገኛል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ ረድኤት አስረሳኸኝ ደግሞ በ20 ግቦች ተከታዩን ስፍራ ይዛለች።
ሀላባ ከተማ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ
May 7, 2026 153
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 29/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ሀላባ ከተማ ጋሞ ጨንቻን በመለያ ምት አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የቡድኖቹ ጨዋታ በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ ወደ መለያ ምት አምርቷል። በዚህም ሀላባ ከተማ 4 ለ 3 በማሸነፍ የዘንድሮው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አሸናፊ በመሆን በበላይነት አጠናቋል። ጋሞ ጨንቻ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። ሁለቱ ክለቦች በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጋቸው ይታወቃል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ደሴ ከተማ የካ ክፍለ ከተማን 1 ለ 0 በመርታት ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። በዘንድሮው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ 21 ክለቦች በሁለት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። አቃቂ ክፍለ ከተማ፣ ሐረር ከተማ፣ ነቀምቴ ከተማ፣ ቦዲቲ ከተማ፣ ሶሎዳ አድዋ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ ወደ አንደኛ ሊግ የወረዱ ቡድኖች ናቸው።
ደሴ ከተማ በከፍተኛ ሊግ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቀቀ
May 7, 2026 134
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 29/2018 (ኢዜአ)፦ በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የደረጃ ጨዋታ ደሴ ከተማ የካ ክፍለ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አማኑኤል ግዛቸው በ68ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ደሴ ከተማ በከፍተኛ ሊግ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። የካ ክፍለ ከተማ አራተኛ ሆኖ ዓመቱን ጨርሷል። ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ያደጉት ጋሞ ጨንቻ እና ሀላባ ከተማ የከፍተኛ ሊግ ዋንጫን ለማንሳት ከቀኑ 9 ሰዓት ከ30 በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
አዲስ አዳጊዎቹ ጋሞ ጨንቻ እና ሃላባ ከተማ የከፍተኛ ሊግ ዋንጫን ለማንሳት ይፋለማሉ
May 7, 2026 145
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2018 (ኢዜአ)፦ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ያደጉት ጋሞ ጨንቻ እና ሃላባ ከተማ የከፍተኛ የሊግ የፍጻሜ ጨዋታቸውን ዛሬ ያደርጋሉ። ጨዋታው ከቀኑ 9 ሰዓት ከ30 ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል። ጋሞ ጨንቻ በምድብ ሀ በ41 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በምድብ ለ የተጫወተው ሃላባ ከተማ በ41 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። ሁለቱም ክለቦች ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ሲያድጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ቡድኖቹ ዓመቱን ሙሉ የተፋለሙበትን የከፍተኛ ሊግ ዋንጫ ለማንሳት ጠንካራ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተያያዘም የካ ክፍለ ከተማ እና ደሴ ከተማ ሶስተኛ ደረጃን ለማግኘት ከቀኑ 6 ሰዓት ከ30 በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል
May 8, 2026 77
ጊምቢ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ በምእራብ ወለጋ ዞን ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታቸው የጎላ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ እንዳሉት በዞኑ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል። ከችግኞቹም መካከል ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታቸው የጎሉ የቡና፣ የአቮካዶ፣ የማንጎ፣ የፓፓያ እና ሌሎች እንደሚገኙበት አስረድተዋል። የችግኝ ተከላው በበጋ ወራት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ፣ ለእንስሳት መኖ እንዲውልና ለም አፈር በጎርፍ እንዳይወሰድ ለመከላከል ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱ ተገልጿል። ይህም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ችግኞቹን በበጋ ወራት በተከናወኑ የተለያዩ የእርከን ስፍራዎችና የተመረጡ ቦታዎች ለመትከልም እስካሁን ከ117 ሚሊዮን በላይ ጉድ ጓዶች ቁፋሮ መከናወኑን አቶ ፍቅሩ ጠቅሰዋል። ስራውን ለማሳካትም አርሶ አደሩን በማሳተፍ መከናወኑን የጠቀሱት ሀላፊው፤ የግብርና ባለሙያች ድጋፍና ክትትል ስራዎች መጠናከራችውን አንስተዋል። ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውን የጠቀሱት ደግሞ የጊምቢ ወረዳ አርሶ አደር ዋኬኔ አምሳሉ ናቸው። ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞችን ጽድቀት መጠን ለማሳደግ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በመንከባከብ ከሰውና እንስሳት ንክኪ መጠበቃቸውን ተናግረዋል። ዘንድሮም በመንግስት ከሚለሙት ችግኞች ባለፈ እሳቸው በግላቸው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞችን ማፍላታቸውን ጠቁመዋል። ከዚህ በፊት ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት ባለመስጠታቸው ያጡትን ምርታማነት በሚያካክስ መልኩ በመጪዉ ክረምት የሚተከሉ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች በብዛት ማዘጋጀታቸው የገለጹት የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ለሊሳ ኤቢሳ ናቸው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በተሰራው ስራ በርካታ ጥቅም በማግኘታቸውም ስራውን ለማስቀጠል ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ልማት ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ አድርጓል
May 8, 2026 118
ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች የክልሉን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረጋቸውን የክልሉ አካባቢና ደን ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢኒሼቲቭ የተራቆቱ አካባቢዎችን አረንጓዴ በማልበስና የአካባቢን ሥነ ምህዳር በማስተካከል አርሶ አደሩን ተጠቃሚ እያደረገ ነው። የአማራ ክልል አካባቢና ደን ጥበቃ ባለስልጣን ሃላፊ ተስፋሁን አለምነህ ለኢዜአ እንደገለጹት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በክልሉ ከተጀመረ ወዲህ በክልሉ የደን ሽፋን ላይ አበረታች ለውጥ ታይቷል። ለዚህም ባለፉት ዓመታት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች የክልሉን የደን ሽፋን ቀደም ሲል ከነበረበት 13 ነጥብ 8 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ማሳደጋቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ልማቱ የተራቆቱ አካባቢዎች በአረንጓዴ እንዲሸፈኑ፣ የአፈር መሸርሸር እንዲቀርና ለምነቱ እንዲጨምር እንዲሁም የከርሰና የገጸ ምድር ውሃ እንዲጨምር አስችሏል ብለዋል። በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በለሙ አካባቢዎች አርሶ አደሩ የእንስሳት መኖን ጨምሮ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ቸግኞችን በመትከል ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱንም አመልክተዋል። በተለይ መርሀ ግብሩ በእንስሳት እርባታ፣ በእንስሳት ማድለብ፣ በወተት ልማትና በንብ ማነብ ሥራ ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ነው ያስታወቁት። በክልሉ ግብርና ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር እስመለዓለም ምህረት በበኩላቸው፣ በዘንድሮ ክረምትም የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል አረንጓዴ አሻራን አጠናከሮ ለማስቀጠል ዝግጅት እየተደረገ ነው። እስካሁንም ዘንድሮ ከሚተከለው አጠቃላይ ችግኝ 94 በመቶ የሚሆነው ተፈልቶ ለተከላ መዘጋጀቱን ጠቁመው፣ ለችግኝ ተከላም ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ተዘጋጅቷል ብለዋል። በአማራ ክልል ባለፈው የክረምት ወቅት ከተተከሉ አጠቃላይ ችግኞች ውስጥ 86 በመቶ የሚሆኑት መጽደቃቸውን በመጀመሪያ ዙር በተካሄደ ቆጠራ መረጋገጡን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
በክልሉ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ከ68 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይሸፈናል
May 7, 2026 240
ቦንጋ፤ሚያዝያ 29/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ከ68 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለመሸፈን ታቅዶ የችግኝ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሀገሪቱ ከፍተኛ የደን ሽፋንና የተፈጥሮ ሀብት ከሚገኝባቸው አካባቢዎች አንዱ ነው። ክልሉ በየዓመቱ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚያከናውናቸው የችግኝ ተከላ ስራዎች፣ ነባር ደኖችን ከመጠበቅ ባለፈ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ለማልማትና የብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። የዘንድሮው የ68 ሺህ ሄክታር መሬት ሽፋን ዕቅድም ይህንን ክልላዊና ሀገራዊ የአየር ንብረት ለውጥ የመቋቋም ስትራቴጂ አካል ያደረገ ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው እንደገለጹት፤ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡ ለዚህም ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች የማዘጋጀትና በቴክኖሎጂ የታገዘ የተከላ ቦታ ልየታና መረጃ የማሰባሰብ ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ከ68 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በደንና በሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ችግኞች ለመሸፈን የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና የስራ እድል በመፍጠር የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት መምሪያ ምክትል ሀላፊና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ታሪኩ ወልደ ሚካኤል በበኩላቸው፣ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ዝግጅት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። በዞኑ የፍራፍሬ፣ የሻይ፣ የቡናና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በ539 የችግኝ ጣቢያዎች ዘር የማፍሰስና የችግኝ እንክብካቤ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። የተዘጋጁ ችግኞችም በ36 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የሚተከሉ ሲሆን ቦታ የመለየት እና መረጃ የማደራጀት ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። አርሶ አደሮችም፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ፀድቀው ውጤት እያሳዩ መሆናቸውን ገልፀው፣ የመርሃግብሩ መጀመር ደንን በአግባቡ ለመጠበቅ ትልቅ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ተከላ መርሃግብር የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል። የሚተከሉ ችግኞች ፀድቀው አገልግሎት እንዲሰጡ መንከባከብ አስፈላጊ መሆኑን የጠቆሙት አርሶአደሮቹ ፣ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በርካታ ጥቅም እያገኙ እንደሆነም ገልፀዋል።
በጉጂ ዞን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተተከሉ ነው
May 6, 2026 173
አዶላ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ በጉጂ ዞን ድርቅና የአካባቢ መራቆትን ለመቋቋም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተከላ መጀመሩን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ ፡፡ በጽህፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ወንዶ ሸርቦቴ እንዳሉት፤ በዞኑ ድርቅና የአካባቢ መራቆትን በዘላቂነት ለመቋቋም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተከላ ተጀምሯል፡፡ በዞኑ ለደን፣ ለጥላ ዛፍ፣ ለፍራፍሬ ልማት፣ ለውበትና ለእንስሳት መኖ የሚውሉ ከ98 ሚሊዮን 800 ሺህ በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ከተዘጋጁት ችግኞች ውስጥ እስካሁን 27 ነጥብ 8 ሚሊዮኑ የበልጉን ዝናብ በመጠቀም በ6 ሺህ 726 ሄክታር መሬት ላይ መተከላቸውን ገልጸዋል። በዞኑ እየተተከሉ ያሉት ችግኞች ድርቅና የአካባቢ መራቆትን ከመቋቋም አልፎ በፍራፍሬ ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ናቸው ብለዋል፡፡ ቀደም ብለው የተተከሉ ችግኞች የእንስሳት መኖና የከርሰና ገጸ ምድር ውሀ አቅርቦትን በማሻሻል የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደጋቸውን ጠቅሰዋል። በዞኑ አዶላ ወረዳ የዳማ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሙሉጌታ አሰፋ በበኩላቸው፤ በአካባቢያቸው የሚስተዋለውን የአካባቢ መራቆትና ድርቅ ለመከላከል በሚከናወኑ ተግባራት በንቃት መሳተፋቸውን አስታውሰዋል። ቀደም ብለው የለሙ አካባቢዎችን ከሰውና እንስሳት ንክኪ በመከለል ለመኖ አቅርቦትና ለንብ ማነብ ስራ ላይ በማዋል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በዘንድሮ የበጋ ወራትም የማሳና የተራራ ላይ እርከን ስራ ላይ ከመሳተፍ ባለፈ በክረምቱ ወቅት የሚተከሉ ችግኞች ማፍላታቸውን ጠቁመዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት ይገባል
Apr 28, 2026 935
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት እንደሚገባ የሕብረቱ ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃጸም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 ጎን ለጎን የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው። የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድን ሀገር በቀል በማድረግ አካታች ዕድገትና ዘላቂ የኢኮኖሚ ሽግግርን የሚያፋጥን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ገልጸዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራትም ብሔራዊ የልማት ዕቅዶችን ከአጀንዳው ጋር በማጣጣም የበጀት ድልድልና የፖሊሲ እርምጃዎችን ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካ አጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦች የበለጸገች አህጉርን እውን ለማድረግም የአባል ሀገራት ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። የአጀንዳ 2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን በማሳካት የተሳለጠ የለውጥ ሽግግርን ለመፍጠርም ጠንካራና የተሰናሰለ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና አህጉራዊ የፖሊሲ ፍሰት ሊኖር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ለዚህም የመንግሥታት፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች በወሳኝ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ የሚኖራቸውን ትብብርና ቅንጅት የሚያበረታታ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የዑጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትርና ተሰናባቿ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ ቢሮ ሊቀ-መንበር ሮቢናህ ናባንጃ በበኩላቸው፤ የአፍሪካውያን ድምፅ በወሳኝ የዓለም መድረኮች ላይ መንፀባረቅ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ መድረኮች በከፍተኛ ደረጃ ከሚደረግ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ባለፈ በወሳኝ ስትራቴጂክ ሂደቶች ላይ በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ብለዋል። የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካትም ሎጂስቲክስ፣ ትራንስፖርትና መሰል የትኩረት ዘርፎች ላይ በስፋት በመሰማራት ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች ነው
Apr 28, 2026 510
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃፀም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 በትይዩ የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው። በአፍሪካ አካታች ዕድገትና ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ሽግግር ለመፍጠር ወሳኝ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድ ሀገር በቀል እንዲሆን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ተናግረዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራት ብሔራዊ የልማት ዕቅዶቻቸው ከአጀንዳው ጋር እየተጣጣመ መምጣቱን በማንሳት፤ የበጀት ድልድልና ፖሊሲዎቻቸው ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ የሰጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን በማሳካት የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ በሀገራት መካከል ያለው ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባም አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸውን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ አለባቸው
Apr 27, 2026 530
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸው ላይ እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከታንዛኒያ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የአፍሪካ ወሳኝ ማዕድናትን ለአረንጓዴ የኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ማዋል" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጁት የ12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ቅድመ ጉባኤ ተካሂዷል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ እንደ ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ግራናይት እና ሌሎች የከርሰ ምድር ሀብቶችን ጨምሮ የዓለምን 30 በመቶ ማዕድናትን ይዛለች፡፡ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻዋን የዓለምን ከፍተኛ የኮባልት ማዕድን የያዘች መሆኑን ገልጸው፤ ይሄውም አፍሪካን የዓለም አቀፍ የኃይል ሽግግር /Energy Transition/ ማዕከል ያደርጋታል ብለዋል፡፡ አፍሪካ ዩራኒዬምና ሌሎች የከርሰ ምድር የከበሩ ማዕድናት ባለቤት መሆኗን በመጥቀስ፤ ለዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል አቅርቦት አስተዋጽኦ ከማድረግ ባለፈ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ኒውክሌር ኃይል ልማት እያመሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አፍሪካ የከበሩ ማዕድናት ባለቤት ብትሆንም አብዛኛው በጥሬ እቃ መልክ ወደ ውጭ የሚላክ በመሆኑ የአህጉሪቱ የእርስ በእርስ ግብይት ከሁለት በመቶ እንዳማይዘል ተናግረዋል፡፡ በአህጉሪቱ የማዕድናት ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን መገንባት ቢቻል በየዓመቱ ከ24 ቢሊየን ዶላር በላይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘትና ለ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ይቻላል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ የማዕድን ፖሊሲ ለእሴት መጨመር፣ ኢንዱስትሪ ልማትና ሁሉን አቀፍ ልማት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአህጉሪቱ የተቀናጀ ቀጣናዊ ኢንዱስትሪ ለመገንባት ያለውን ፍላጎት በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አህጉራዊ የማዕድን ሀብቶችን ወደ ዘላቂ ብልጽግና መለወጥ ይገባል ብለዋል፡፡ በዚህም የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቀጣናዊ እሴት ሰንሰለትን በማጠናከር የማዕድን ጸጋዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚደረገው ጥረት ትብብሩን ማጠናከሩን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካዳሪ ሲንጎ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍና አካታች ዕድገት ለማስመዝገብ የማዕድን ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በተፈጥሮ ሀብታችን ላይ የሚኖረን ትብብርና ተሳትፎ ስትራቴጂያዊና መዳረሻ ግብ ያለው መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮት ሽግግርን ለመፈጠር በአቅም ግንባታ ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 916
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ሐተታዎች
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 230
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች
May 3, 2026 395
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር እያሸጋገራት ይገኛል።የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የመሰረተ ልማት እና የተቋማት ግንባታ ስራዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋንኛ ስራዎች ናቸው። ለውጡን ተከትሎ መንግስት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን ስትራቴጂ በመቅረጽ የዲጂታላይዜሽን ስራውን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶ አድርጎታል። የለውጡ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ ቴክኖሎጂን እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመቁጠር "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን አጠቃላይ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ተግባር ገባ።ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱን የዲጂታል ጉዞ ከመሰረቱ የለወጠ ሲሆን፣የመጀመሪያው ትልቅ እርምጃም የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ነበር። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ የኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል።በተለይም የአምስተኛ ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን አስችሏታል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ለውጡ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ውጤት አምጥቷል።እንደ ቴሌብር (telebirr) ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ምንም የባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ፣ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር ትልቅ መደላድል ፈጥረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ አድማስ ይበልጥ አስፍተውታል። የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ራዕይ ለዓለም ያሳየችበት አጋጣሚ ነው።ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የካንሰር ህመምንና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ መለየት የሚያስችሉ የኤአይ ውጤቶችን አበልጽጓል። በግብርናውም ረገድ የአፈርን ለምነትና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ዋስትና ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል ዓለም ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የፋይዳ (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን መረጃ በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የለውጡ ፍሬያማነት ማሳያ ነው።የሳይንስ ሙዚየምም የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያሳይና የሀገሪቱን ቴክኖሎጂ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ሆኗል።የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቅርቡ መጠናቀቁ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2025 ስትራቴጂው መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዲጂታል 2030ን ይፋ ሲያደርጉ የነበረው ትልቁ መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች የሚል ነው። ስትራቴጂው በዋናነት"የፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት፣ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠር፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) አድርጎ መገንባትን እንደ ዋነኛ ግብ አስቀምጧል። ይህም ሁሉን አቀፍ የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ የመንግስት አገልግሎቶችን መቶ በመቶ ወረቀት አልባ በማድረግ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) በግብርና፣ በጤናና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ በስፋት በመተግበር የምርታማነት አብዮት መፍጠርን ያለመ ነው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ስራ በአህጉራዊ ደረጃ ያለውን ተቀባይነትና የተሰጣትን ትልቅ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት የቴክኖሎጂ ከፍታ፣ ሀገሪቱን በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ተፎካካሪ ብቻ ሳይሆን የፈጠራ ምንጭ እንድትሆንም እያደረጋት ይገኛል። በዚህ ረገድም የቀጣዩ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ስኬትም ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና በቴክኖሎጂ የበለጸገች ሀገር የማድረግ ራዕይን ለማሳካት እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ ያገለግላል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 3, 2026 266
ክልሎች፤ሚያዝያ 25/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮች በወፍ በረር ሲቃኙ ይህንን ይመስላሉ!!! 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡትን የቶዮ ሶላር ኢነርጂ ምዕራፍ ሁለት፣ የኦሪጂን እና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካን በይፋ መርቀዋል። እነዚህ የሶላር ፋብሪካዎች በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን፣ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅን እና 7 ቶን ሃይድሮጅን ለገበያ ያቀርባል። ይህ ክንውን የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ለማፋጠን፣ የኢነርጂ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ዘላቂ፣ የማይበገር ሁለንተናዊ እድገት ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል። 👉እንቁላልን ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት የማቆየት ልምምድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ፤ የዶሮ እንቁላል ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት ያህል ማቆየት የሚያስችል ቴክኖሎጂን ወደ ተግባር ለማስገባት ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል። በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ሕክምናና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ማስተዋል ብርሃን፤ ዩኒቨርሲቲው የእንቁላል ምርት ብክነትና ብልሽትን ለማስቀረት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። በዚህም እንቁላልን እስከ ሁለት ዓመት ያለ ምንም ብልሽት ማቆየት የሚያስችለውን ቴክኖሎጂን የማላመድና የማስተዋወቅ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂው በአንድ ሊትር ውሃ ውስጥ 30 ግራም የኖራ አፈር ወይም ላይም ስቶን ጨምሮ በማዋሃድ እስከ 12 እንቁላሎችን ሳይበላሽ የሚያስቀምጥ በመሆኑ ለአርሶ አደሩ ተመራጭ ነው ያሉት። ይህም እስካሁን ባለው አንድ ትኩስ እንቁላል ሳይበላሽ መቆየት የሚችለው እስከ ሁለት ሳምንት መሆኑን ጠቁመው ቴክኖሎጂው ይሄን ችግር በመሰረታዊነት የሚቀይር ነው።፡ ቴክኖሎጂውን በስፋት በማስተዋወቅና በማላመድ ረገድም ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን በመስጠት ችግር ፈቺነቱን የማሳየት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። 👉የአፋር ጥጥ ተስፋ ሰጪ ፀጋ! የአፋር ክልል የበርካታ የተፈጥሮ ፀጋዎች ባለቤት ነው፤ ሆኖም እነዚህን እምቅ ሀብቶች ወደ ልማት በመቀየር ከፀጋዎቹ ተቋዳሽ ለመሆን ሳይቻል ለረጅም ተቆይቷል። አሁን ግን ከፀጋዎቹ አንዱ የሆነውን ተፈጥሯዊ ጥጥ (Organic Cotton) ለማምረት ተስፋ ሰጪ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በሰመራ በተካሄደ የውይይት መድረክም በግብርና ሚኒስቴር የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳምሶን አሰፋ፤ የአፋር ክልል ጥጥን በመስኖ ማልማት የሚቻልበት አቅም ያለው በመሆኑ ልማቱን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሀገራችን የጥጥ ልማትን ለማስፋፋት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው፤ ባለፈው የምርት ዘመን እንደ ሀገር በስድስት ክልሎች 110 ሺህ ሄክታር መሬት በጥጥ መልማቱን ተናግረዋል።በዚህም 79 ሺህ ሜትሮክ ቶን የተዳመጠ ጥጥ በማምረት ለኢንደስትሪዎች ማቅረብ እንደተቻለ ነው የገለፁት። 👉የሸማቹ ሸክም ይቀላል! የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ስድስት ከተሞች ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ ሲያካሄድ የህብረት ስራ ማህበራት ከእንግዲህ የሸማቹን ሸክም ሊያቀሉ ይገባል የሚል ሀሳብ ተነስቷል። በሀዋሳው በተካሔደው የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለያዩ መስኮች የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊት ሀገር ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን አንስተዋል። በተከናወኑ ተግባራትም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አክለዋል። የመንግስትን፣ የግሉ ዘርፍንና የዜጎችን የካፒታል አቅምና ዕውቀትን ደምረው የያዙት የህብረት ስራ ማህበራት ግብርናውን በማሻገር የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት በመቀየር ረገድ ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልፀው የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመፍታትና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር የሸማቹን ህብረተሰብ ሸክም ያቀላሉ ተብሎ እንደሚታመንም አስረድተዋል። 👉ምርምር ለቀጣናዊ ትስስር በጅማ ዩኒቨርሲቲ "ቀጠናዊ ሰላምና ትብብር ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ባለችበት ቀጣና የሚታዩ ፍላጎቶችን ለማሟላትና ተግዳሮቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመፍታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ተነስቷል። በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጦሽኔ ቀጣናውን በልማት ለማስተሳሰር በሚደረግ ጥረት የትምህርት ተቋማቱ የጥናትና ምርምር ድጋፍ ከፍተኛ ሚና አለው ያሉ ሲሆን ለዚህም ተቋማቱ ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያሳድጉ እና ማህበራዊ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚያግዙ የፖሊሲ መነሻ ሀሳቦችን በጥናትና ምርምር እንዲያፈልቁ አሳስበዋል። የሚወጡ ጥናቶች በቀጣናው በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ እየተከሰቱ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሊሆኑ እንደሚገባ የተጠቀሰ ሲሆን ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን በመተግበር እያከናወነች ያለችው ተግባር በተመክሮነት ቀርቦ አድናቆትን አስገኝቶላታል። 👉ሻይ ቅጠል አሁን አሁን አርሶ አደሩ በተለያዩ ኢንሼቲቮች በሚከናወኑ የግብርና ልማት ትግበራዎች ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። በርካታ አርሶ አደሮች በሻይ ቅጠል ልማት ኢንሼቲቭ በመሰማራት ገቢን ከማሳደግ ባለፈ ለሌሎችም ሰፊ የስራ ዕድል እየፈጠሩ ይገኛሉ። በጅማ ዞን የሻይ ቅጠል ልማትን ከማስፋፋት ባለፈ የበያ ትስስር የመፍጠርና ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለፋብሪካ ለማቅረብ ለአርሶ አደሩ ግንዛቤ እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም፤ በዞኑ የሻይ ቅጠል ልማትን በኢኒሼቲቨን መልክ በመተግበር የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድል እየተፈጠረ ነው። ዘንድሮም ስራውን ለማስቀጠል በተመረጡ 6 ወረዳዎች በመጪው ክረምት የሚተከሉ 50 ሚሊዮን ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን ህዝብን በማሳተፍም ወደ 2 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬትን ለመሸፈንም ታስቧል። ጥቅሙ የገባቸው አርሶ አደሮችም የሰብል ልማቱን ለጊዜው ተወት በማድረግ በሻይ ቅጠል ልማት ላይ እየተሳተፉ እንደሆነ ይናገራሉ። በዞኑ የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አርሶ አደር ሲራጅ ሼክ ከድር በሻይ ቅጠል ልማት ላይ መሳተፍ ከጀመሩ ወዲህ ገቢያቸው መጨመሩን ተናግረዋል። አርሶ አደር ሱልጣን አባሞጋ በበኩላቸው ተሰማርተውበት ከነበረው የሰብል ልማት ወደ ሻይ ቅጠል ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአካባቢ ፀጋን ተገንዝቦ ወደ ስራ መግባት ተጠቃሚነትን እንደሚያመጣ ማሳያ ሊሆን ይችላል። 👉ተስፋዎች ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በሆሳዕና ከተማ የተካሄደው የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ደረጃ ሽግግር እውቅና መርሃ ግብር ይጠቀሳል። "የኢንተርፕራይዞች ሽግግር ለእመርታዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ የተከናወነው የዕውቅና መድረክ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት ነው የተካሄደው። እሳቸው እንደገለፁት፤ ኢንተርፕራይዞቹ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ ነው። በክልሉ በገጠርና በከተማ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ ከ25 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ መስኮች መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በጥቃቅንና በአነስተኛ ደረጃ የሚገኙ 4 ሺህ 948 ኢንተርፕራይዞችን የማሸጋገርና 495 ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን የመለየት ስራ መሰራቱም እንዲሁ። ከኢንተርፕራይዝ ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሸጋገሩ አምራቾች እንደተናገሩት ሽግግሩ ስራቸውን በተሻለ ሁኔታ ለመከወን እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል። 👉ትምህርትና አርብቶ አደሩ የወፍ በረር ቅኝታችንን ስንቀጥል ጋምቤላ እንደርሳለን፤ በሳምንቱ በጋምቤላ ከተማ በተካሄደ መድረክም የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውም ተመልክቷል። በለውጡ ዓመታት የአርብቶ አደሩን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ውጤት መመዝገባቸውም እንዲሁ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም ረገድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና የገዘፈ መሆኑም በመድረኩ መገለፁን ቅኝታችን ዳሶታል። 👉ልወቅሽ ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ጠቅለል አድርጎ የዳሰሰው ቅኝታችን ደግሞ በስድስት ከተሞች ለማካሄድ ዕቅድ የተያዘለትና እስካሁን በጅማ፣ በሀዋሳና በደብረ ብርሃን ከተሞች የተካሄደው የ"ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ታላቁ ሩጫ" ከተሞቹን ከማስተዋወቅ የዘለለ ፋይዳውን በመርሃ ግብሩ ላይ በተላለፉ መልዕክቶቹ አሳይቷል። ለአብነት በጅማ የተካሄደው ‘ፖሊዮን በጋራ እናጥፋ’ የሚለውን የጤና ጉዳይን ያነሳ ነበር። በአዳማ ከተማ የተከናወነው ሁነት ደግሞ በመኪና ውድድር ታጅቦ የተከናወነና የቱሪዝም መስህቦችን ማስተዋወቅን ታላሚ ያደረገ ነበር። ‘’ለሀዋሳ ከፍታ እንሮጣለን’’ በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ሁነትም ከጅማና አዳማው ሁነት የተለየ እሳቤንም ሆነ መልዕክትን አልያዘም። ሁሉም ሁነቶች ከዋነኞቹ አምስት ምጣኔ ሃብታዊ አምዶች መካከል አንዱ የሆነውን ቱሪዝም ልማት በማጠናከር የማህበረሰቡን የዘርፉ ተጠቃሚነት ማላቅን ታሳቢ ማድረጋቸውን መመልከት ተችሏል። ቅኝቶቻችን በወፍ በረር ይህንን ይመስላሉ!! የሳምንት ሰው ይበለን!!!
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 26, 2026 642
ክልሎች፤ሚያዝያ 18 /2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር የምንቃኝበት ነው። በዚህ ሳምንትም አንኳር የክልሎች ክንውኑን የሚያሳዩ መረጃዎች ቀርበዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተም! ኢትዮጵያ የበጋ መስኖ ልማት ስራ መደባኛ ስራዋ ካደረገች ወዲህ አያሌ ለውጦች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ባለፉት ዓመታት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በእቅድ እና በቁርጠኝነት በመከናወኑ ከውጪ የሚገባ ስንዴ ቀርቷል፤ የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጥረቱም ቀጥሏል። ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚደረገው ሽግግርም ዓመቱን ሙሉ በማልማት እየታጀበ ሲሆን የአንበሳውን ድርሻ የሚይዘው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሥራ ነው። በዚህ ውስጥ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አበረታች ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በተያዘው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ወሬርሶ ማሊማ፣ በጂዳ ወረዳ ሲባ ሲርቲ እና ቂምቢቢት ወረዳ ሰገሌና ደርማሙሳ ቀበሌ በኩታ ገጠም የለማ እና በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ የስንዴ ቡቃያ አስቃኝተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፎቶ ጋር ያያዙት መልዕክትም ''ይህ የበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት በምግብ ራስን የመቻል እና የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተማችን ነው'' ይላል። ብሪክስ -- ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በባህር ዳር ከተማ ''የብሪክስ አሁናዊ አቅሞች እና የኢትዮጵያ የልማት ትብብር ትኩረቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ጉባኤ አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ በመሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑ ይታወቃል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሐመድራፊዕ አባራያ በመድረኩ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ሳትፎዋን በማሳደግ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የተደራጁ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። መድረኩም ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችላት የሁለትዮሽ ትብብር ጭምር የተካሄደበት፤ በብሪክስ ማዕቀፋ በተለይም በግብርና እና ስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና መሰል ዘርፎች ልምድ የተሰጠበትም መሆኑ ተመላክቷል። ማረም እና ማነጽ የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል እንዲሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት መሰጠቱ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነው። የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነሮች የጋራ ጉባኤ “የማረሚያ ተቋማት ለሀገር ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል ሆነው እንዲያገለግሉ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከታራሚዎች የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የመሰረታዊ ፍላጎት አቅርቦት፣ ከማረሚያ ቤት የሪፎርም ሥራዎች እንዲሁም ከማረም የማነጽ ተሃድሶ ልማት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ጉባኤው በልዩ ሁኔታ የመከረበት ነው። ኢትዮጵያ ማምረቷን ቀጥላለች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የራስን አቅም የመገንባት ታሪካዊ ጉዞ እንደቀጠለ ነው። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል "ድሬ ታምርት ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ በተዘጋጀ የአምራች ኢንዱስትሪ ኤክሲፖ ላይ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ በተደረገው ድጋፍና ክትትል እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በንቅናቄው የተዘጉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲመለሱ በማድረግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በጥራትና በስፋት እየተተኩ ነው ብለዋል። ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድም መሠረታዊ ውጤቶች ተገኝተዋል ነው ያሉት። ዘንድሮ ብቻ 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ የውጭ ሀገራት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት መዘጋጀታቸውም ተገልጿል። ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል በኢትዮጵያ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ውኃ የህልውና ጉዳይ ነው። በእርግጥ ለፍጡራን ሁሉ ውኃ ህይወት ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ግን ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል። በሳምነቱም በአፋር ክልል ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የአይሳኢታ አፋምቦ የብዙሃን መንደር እና የአይሳኢታ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተከናወነው ልማት የህብረተሰቡን ጥያቄዎች በተግባር ከመመለሱ በላይ፣ በየደረጃው ያለውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፤ መንግስት የውሃ ሽፋን አነስተኛ ለሆነባቸው አካባቢዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት፣ በፕሮጀክቶች ታግዞ መስራት እንደሚገባ በጽኑ ያምናል፤ በተለይም የለውጡ መንግስት ለቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች በሰራው ስራ የውኃ ተደራሽነት በእጅጉ ማደጉን አንስተዋል። ልምድ ልውውጥ እና ተሞክሮ -ለምክር ቤቶች ሌላው ቅኝታችን በዚህ በተጠናቀቀው ሳምንት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤትና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ መካሄዱን የዳሰሰ ነው። የጋራ የምክክር መድረኩ ዓለማ የልምድ ልውውጥና የልማት ሥራዎችን በመመልከት ተሞክሮ መለዋወጫ ነው።የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ፤ መንግስት ሕዝቡ የሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የምክር ቤቶችን አደረጃጀት ማጠናከርና የክልሉ ሕገ መንግስት ያስቀመጣቸውን ኃላፊነቶች መፈጸም ይገባል ብለዋል።የመንግስት የልማት ኢኒሼቲቮች የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል የሚያስችሉ በመሆናቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መተግበር እንዲችሉ ምክር ቤቶች ያለሰለሰ ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተመልክቷል። የጤና ልማት ስራ እስከ አክሞ ማዳን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ በሚደረግ ጥረት የአጋር ድርጅቶች አስተዋጾ ትልቅ ድርሻ እንዳለውም የተመለከተው በዚህ ሳምንት ነው። ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጋር በመሆን በአርባ ምንጭ ከተማ ያስገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ መሰል የጤና ዘርፍ የልማት ስራዎች መንግስት በዘርፉ የያዘውን ውጥን ከማሳካት አንጻር እገዛቸው ትልቅ መሆኑን አንስተዋል።ማዕከሉ ማህበረሰቡ በቅርበት ሕክምና እንዲያገኝ ከማስቻል ባለፈ ወደ ሌላ አካባቢ ሄዶ ሲታከም ሊያወጣ የሚችለውን ወጪ ያስቀራል። ማዕከሉ የኩላሊት እጥበት ማሽኖች፣ የመድሃኒት ቤት፣ መኝታ አልጋዎችና የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሟልቶ የተገነባ መሆኑም ታውቋል። የከተሞች ኮሪደር- ከቱሪዝም እስክ ኮንፍረንስ ማዕከልነት በኮሪደር ልማት እጅግ ከተዋቡ እና ከደመቁ የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል ሀዋሳ አንዷ ናት። በሳምንቱ የከተማዋ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ማጠናቀቂያ የምስጋናና ዕውቅና እንዲሁም የአራተኛ ዙር የኮሪደር ልማትና የሐይቅ ዳርቻ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄዷል፡፡ የሲዳማ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርቡ ቀጥሏል ብለዋል። በቀጣይ ለሚከናወነው የኮሪደር እና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ስራዎች እንደሚቀጥሉ አንስተው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጎላ መሆኑን ገልፀዋል። የከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነት ለማጠናከር ሥራዎች በላቀ ፍጥነትና ጥራት መከናወናቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ምርጫ -የዴሞክራሲ መሰረት ሳምንቱ በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ከመጠናቀቁ በፊት መራጮች የምርጫ ካርድ ወስደው ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹበትም ነበር። ኢትዮጵያዊያን መጪውን ጊዜ የተሻለ የሚያደርግላቸውን መንግስት ለመመረጥ ዝግጅታቸውን በተግባር እያረጋገጡ ነው።
ትንታኔዎች
የ471 ሚሊዮን ተከታዮች ባለቤት የሆኑ የ30 ሀገራት ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሳተፉበት ታሪካዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ
May 6, 2026 248
በመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) ላይ ለመሳተፍ፣ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡና በአጠቃላይ 321 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 61 ታዋቂ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ወደ አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። እነዚህንም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 120 ታዋቂ ኢትዮጵያውያን የማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ፈጣሪዎች ይቀላቀሏቸዋል። ታሪካዊው ጉባኤ ነገ እና ከነገ በስቲያ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ጉባኤው በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እና በኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ የጋራ ትብብር የተዘጋጀም ነው። በአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከል አዲስ አበባ የሚካሄደው ይህ ጉባኤ የአፍሪካን ዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ እንደገና ለመቅረጽ ያለመ ነው። ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበር እና የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅበት ስም ነው) ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገብቷል። ሴራሊዮናዊው ቦይዜ ክሪሽ፣ ቤኒናዊቷ ሬጌ ቦይዘር፣ ሴኔጋላዊው ጃው ኬቹፕ እና ስዊዛላንዳዊው ጎጎ እስዋቲኒ ኤምኤም ሌሎች ለጉባኤው የገቡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖፐ ፈጣሪዎች ናቸው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎቹ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል። ጉባኤው በአፍሪካ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሰባሰቡበት፣ ስለራሳቸውና ስለ አፍሪካ የሚናገሩበት፣ እንዲሁም ስለ ይዘት ፈጠራና ስለሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች የሚወያዩበት መድረክ ነው። ይህም ተጽእኖ ፈጣሪዎቹን በአንድ መድረክ የማገናኘት ትልቅ አጋጣሚን ፈጥሯል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በመጠቀም የይዘት ፈጣሪነት የወደፊት ሁኔታ፣ የአፍሪካ አዎንታዊ ገጽታን መገንባት እና የዲጂታል ተጽዕኖን ከአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ጋር ማጣጣም በሚሉ ጉዳዮች ላይ ሶስት የከፍተኛ ደረጃ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ጉባኤው "በችግር ላይ የተመሰረተ" ዘገባን በእውነተኛ የአፍሪካ የዕድገት ታሪኮች ለመተካት የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑም ተመልክቷል። የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ የኢትዮጵያን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ የማስተዋወቅ እድሉ ሰፊ ነው። እነዚህ የይዘት ውጤቶች የአፍሪካን መልካም ገጽታ ለዓለም፣ የኢትዮጵያንም መልካም ገጽታ ለአፍሪካውያን ማሳየት የሚችሉ ናቸው። ጉባኤው ሐሙስ ዕለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚጀመር ሲሆን፣ ከ470 ሚሊዮን በላይ የዲጂታል ተከታዮች አይኖች በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ላይ አርፈዋል። ይህም አፍሪካ የራሷን ታሪክ ራሷ መተረክ የጀመረችበት አዲስ ዘመን ማሳያ ሆኗል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 2, 2026 599
ከሚያዝያ 18 እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአዲስ አበባ በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘውን "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የጎበኙ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ይህ ፋብሪካ በ2025 ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ያድርጉ ፎረም (Invest in Ethiopia Forum) አማካኝነት በተፈረመው ስምምነት መነሻ በ100 ሚሊየን ዶላር የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የተቋቋመ ነው ብለዋል። በውጤታማ ድጋፍ እና ክትትል በስድስት ወራት ብቻ እውን የሆነው "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻ ዘመናዊ ማሽኖች እና በቴክኖሎጂ የተዋቀረ መሆኑን ገልጸው፣ ማምረቻው ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድልም ፈጥሯል ነው ያሉት። በመጀመሪያ ምዕራፍ 2 ጌጋዋት ዓመታዊ የማምረት ዐቅም ያለው ፋብሪካው የኢትዮጵያን የኃይል ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ከታዳሽ ኃይል ለማድረግ ለተጀመረው ሀገራዊ ርዕይ እውን ለማድረግ ተደማሪ ዐቅም ፈጥሯል ሲሉም ተናግረዋል። በተጨማሪም በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ የሚገኘውን የጫማ ማምረቻ እና ንዑስ የኤሌክትሪክ ጣቢያን ተመልክቻለው ብለዋል በመልዕክታቸው። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአራዳ ፓርክን መመረቃቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት አራዳ ፓርክን በመረቁበት ወቅት፤ ፓርኩ አዲስ አበባን ለመለወጥ ያለንን ርዕይ በተግባር ያሳየንበት አንዱ ሥራችን ነው ብለዋል። ቀደም ሲል ተዘንግቶና ለአደጋ ተጋልጦ የነበረው የአራዳ አካባቢ፤ ዛሬ ተመልሶ ተገንብቶ አስደናቂ የከተማ አካል መሆን ችሏል ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለእኛ በምናብ የምትሳል ህልም ብቻ ሳትሆን በተግባር የምትገነባ እውነታ ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጤናማ፣ ጽኑ፣ ለመጭው ትውልድ ተስፋን ከተጨባጭ ሀብት ጋር የምትሰጥ፣ በአፍሪካ መሪ፣ በዓለም መድረክ ደግሞ ተወዳዳሪ የሆነች ሀገር እየገነባን እንገኛለን ብለዋል። በየቀኑም ተስፋን ወደ እውነታ የመለወጥ ተግባራችንን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ሐሳባቸውን ያጋሩበት “የማኅበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀውና በማኅበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የቀረቡበት የምክክር መድረክ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የማኅበራዊ ዘርፍ ግንባታ እንደ ሌሎች መሠረተ-ልማቶች ውጤቱ ወዲያው የሚታይና የሚጨበጥ ባይሆንም፤ ለሀገር ዘላቂና ወሳኝ መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በሚገጥሟት ተግዳሮቶች ሳትገደብ ከሚገመተው በላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተገነባች መሆኗን ገልጸው፤ ምንም እንኳ የዐቅም ውስንነቶች ቢኖሩብንም ለማሻሻል ያልተሞከረ የማኅበራዊ ዘርፍ የለም ሲሉም አስረድተዋል። በየዘርፎች የታለመው ሁሉ በተግባር እንዲተረጎምና ተገቢውን ዓላማቸውን እንዲያሳኩ ብዙ ሥራ ይጠበቅብናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም አንድ እጅ ብቻውን ማጨብጨብ እንደማይችል ሁሉ፤ መንግሥት የሚጀምራቸውን ሥራዎች ሌላው የማኅበረሰብ ክፍል እንደ አንድ ባለ ድርሻ ኃላፊነት ወስዶ በጋራ መቆም እንዳለበት አስገንዝበዋል። • የሞዛምቢክ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት የሞዛምቢክ ፕሬዚዳንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በክብር ተቀብለዋቸዋል። የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጋራ ልማትና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ትርጉም ባለው መልኩ ሊለውጡ የሚችሉ ተጨባጭ ሥራዎችን ቅድሚያ የሰጠ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለእውነተኛ አፍሪካዊ አጋርነት ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ መሆኑንም አስረድተዋል። ከዚያም ባደረጉት ቆይታ ዘላቂ እና ተጨባጭ ለውጥ ለሚያመጣ አጋርነት መሠረት የጣለ ፍሬያማ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በስትራቴጂካዊ ዘርፎች ያለንን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩና የአሠራር ማዕቀፍ የሚሆኑ ልዩ ልዩ የመግባቢያ ሠነዶችን ልውውጥ አካሂደናል ብለዋል። • የበጋ መስኖ እርሻ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የበጋ መስኖ እርሻ በምግብ ራሳችንን ለመቻል በሚደረገው ጉዞ ውስጥ የጸና መሠረት የጣልንበት ምዕራፍ ነው ብለዋል። የውኃ ሀብታችንን በአግባቡ በመጠቀም፣ ባልተቋረጠ ጥረት እና ቁርጠኝነት፣ የመልማት ጉዟችን አስተማማኝና ዘላቂ የሆነ የምግብ ዋስትና ወደምናረጋግጥበት ብሩህ ተስፋ እንደሚያሸጋግረን ጥርጥር የለውም ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሆሞሻ ወረዳ የሚገኘውን ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት ጎብኝተዋል። ጉብኝታቸውን ተከትሎም፤ ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት በኢትዮጵያ የግሉን ዘርፍ ያሳተፈ የግብርና ሥራ እንዲስፋፋ ለሚደረገው ሥራ አንድ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ በግል ባለሀብት እየለማ ያለው የግብርና ሥራ እንደ ሶላር ያሉ የኃይል አማራጮችን እና የከርሰ ምድር ውኃን በመጠቀም በመስኖ በማልማት ኢትዮጵያ ለጀመረችው የግብርና ልማት እና የገጠር ሽግግር ሰፊ አስተዋጽኦ ያበረክታል ሲሉም ገልጸዋል። በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግራናይት የሚያመርተውን የኦርላመንት (3ኤም) ማርብልና ቴራዞ ማኑፋክቸሪንግ የሥራ እንቅስቃሴ የጎበኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት የግሉ ዘርፍ በማዕድን ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፍ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ፣ ማበረታቻና ድጋፍ እንዲህ ያሉ ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ ነው ብለዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከወርቅ እስከ ግራናይት በተፈጥሮ የታደለ መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ፀጋ ለሀገር ብልጽግና ለማዋል የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ይበልጥ እንዲጠናከሩ የፌደራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 694
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ጤና ከሀገር በቀል ስኬት ወደ አህጉራዊ መሪነት
Apr 23, 2026 642
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ እያከናወነች ያለችው ስራ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂካዊ የሆኑ ተቋማዊና የፖሊሲ መሰረቶች ተጥለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መቋቋም ለሀገራዊ ችግሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ መፍትሄ ለማግኘት ትልቅ አቅም የፈጠረ ሲሆን፣ ብሄራዊ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ ተቀርጾ መጽደቁ ደግሞ የዘርፉን ልማትና አጠቃቀም በተደራጀ መንገድ ለመምራት አስችሏል። እነዚህ እርምጃዎች ሀገሪቱ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እና 2030 ስትራቴጂ ውስጥ ቴክኖሎጂውን እንደ ቁልፍ የለውጥ አቅጣጫ እንድትጠቀም በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ዘላቂ ለማድረግም በሰው ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በኮዲንግ፣ በዳታ ሳይንስ እና በክህሎት ለማሰልጠን የተጀመረው ግዙፍ ፕሮግራም የለውጡ አንቀሳቃሽ ኃይል እየሆነ ነው። ከዚህም ባለፈ፣ በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ እንዲገነባ መታቀዱና በዚህ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባልነት ውስጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት እንዲሳተፍ መወሰኑ፣ ሀገሪቱ ቴክኖሎጂውን ለውሳኔ ጥራትና ለምርምር በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀመችበት መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ እንደገለጸው፣ ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በሹመት ደብዳቤው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ AI ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አክሎ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የAI አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል እና በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ለሀገራዊ ለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ በዝርዝር አስፍሯል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የAI ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የተያዘው ሥራ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክርም ተገልጿል። ይህ አህጉራዊ እውቅና በተለይ በጤናው ዘርፍ የታዩ ውጤቶችን ያካትታል። ኢትዮጵያ በኤአይ የታገዘ ዲጂታል ኤክስሬይን ለሳንባ ነቀርሳ ምርመራ ካዋሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። በተጨማሪም የ"HEP Assist" መተግበሪያን በሙከራ ደረጃ በማስጀመር፣ በገጠር የሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ውስብስብ ምልክቶችን ሲያዩ ሙያዊ የሕክምና ውሳኔ እንዲሰጡ ድጋፍ እየተደረገ ነው። እነዚህ የዲጂታል ጤና ስራዎች በ7 ክልሎችና በ15 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ መጀመራቸው፣ ቴክኖሎጂው በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የአገልግሎት ልዩነት ለማጥበብ ያለውን ፋይዳ ያሳያል። በአጠቃላይ፣ የኤአይ ቴክኖሎጂ በጤናው ዘርፍ ከሚሰጠው የጡት ካንሰር፣ የአንጎል እብጠትና የቆዳ በሽታዎች ምርመራ ባለፈ፣ በግብርና፣ በፋይናንስና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥም በስፋት እየገባ ይገኛል። በ2030 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ሆስፒታሎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል አገልግሎት ለመቀየር የተቀመጠው ግብ፣ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የጀመረችውን የቴክኖሎጂ ነጻነትና የመሪነት ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓት በጤና፣ በግብርና እና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በጤናው ዘርፍ እንደ ካንሰር እና ሳንባ ነቀርሳ ያሉ በሽታዎችን ቀድሞ በመለየት የህክምና ጥራትን ሲያሻሽል፣ በግብርናው ደግሞ የሰብል ተባዮችንና የቡና በሽታዎችን በመለየት ምርታማነትን እያሳደገ ነው። ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂው በመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ እና በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ሰፊ የመረጃ ትንታኔዎችን በፍጥነት በማከናወን፣ የሥራ ፍጥነትን እና የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል። የዘርፉ ፋይዳ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባለፈ የሀገሪቱን የዲጂታል ሉዓላዊነት እና የሰው ኃይል አቅም በመገንባት ላይ ያተኩራል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶችን በኮዲንግ እና በዳታ ሳይንስ በማሰልጠን እንዲሁም የፈጠራ ማዕከላትን (Startups) በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በሌሎች ላይ ጥገኛ ከመሆን ወጥታ የራሷን የዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ይህም በአህጉር ደረጃ ለሚደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች እንደ አርአያ በመሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ ፍትሃዊነት የመጠቀም ጥቅል ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አድርጎታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሹመት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ ያጎላል። በተጨማሪም ሹመቱ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና አፍሪካ በኃላፊነትና በፍትሐዊነት በታጀበ የኤአይ አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንድትሆን የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣም ያደርጋታል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 4587
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 3044
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8837
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 7321
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 883
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 945
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።