ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በክልሉ ግብርናን ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች ተመዝግበዋል
Dec 9, 2025 22
አዲስ አበባ፤ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ግብርናን ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ። አቶ አወሉ አብዲ በኦሮሚያ ክልል ሸሜን ሸዋ ዞን ደብረሊባኖስ ወረዳ በኩታ ገጠም በመኸር እርሻ የለማን ስንዴ መሰበስብ አስጀምረዋል።   በዚሁ ወቅት በሰጡት ማብራሪያ በክልሉ ዘመናዊ የግብርና የእርሻ ማሽነሪዎች በመጠቀም በተሰሩ ስራዎች ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ላይ ትልቅ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። በዚህም ከተረጂነት በመላቀቅ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ እመርታ እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ ስንዴን ማምርት ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይህም የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የእርሻ ሥራ ከባለፉት ዓመታት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።   ግብዓትን ጨምሮ የሚስተዋሉ ሌሎች ማነቆዎችን በመፍታት በግብርናው ዘርፍ እመርታን ለማምጣት ያስቻሉ ስራዎች ተመዝግበዋል ብለዋል። ስንዴ ልማት ምርት በየጊዜው እየተሻሻለ እንደሚገኝ ገልፀው፤ አርሶ አደሩ የበጋ መስኖ ስንዴን በኩታ ገጠም እና በመስኖ በማልማት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአጠቃላይ የገጠር ሽግግርን በማሳለጥ የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመቀየር የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በዞኖቹ እየተተገበረ የሚገኘው የሻይ ልማት ኢኒሼቲቭ ለገጠሩ ማሕበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ተስፋ የሚጣልበት ነው
Dec 9, 2025 19
መቱ ፤ሕዳር 30/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በጅማ፣ ቡኖ በደሌና ኢሉአባቦር ዞኖች እየተተገበረ የሚገኘው የሻይ ልማት ኢኒሼቲቭ ለገጠሩ ማሕበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ተስፋ የሚጣልበት መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ ተናገሩ። በዞኖቹ ባለፉት ሁለት ዓመታት የተተከሉት የሻይ ችግኞች በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን በማንሳት በመጪው ክረምት የሚተከል የሻይ ችግኝ ዝግጅት ከወዲሁ መጀመሩን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ናቸው።   በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ መንግስት የስራ ሀላፊዎች በኢሉባቦር ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የተለያዩ የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ነው። አቶ ነመራ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በምዕራብ ኦሮሚያ ሶስት ዞኖች እየተተገበረ የሚገኘው የሻይ ልማት ተስፋ ሰጪ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተለይም በጅማ፣ ቡኖ በደሌ እና ኢሉ አባቦር ዞኖች በኢኒሼቲቭ መልክ እየተገበረ የሚገኘው የሻይ ልማት ለገጠሩ ማሕበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ተስፋ የሚጣልበት ነው ብለዋል። በኢሉአባቦር ዞን በሀሉ ወረዳ ባለፉት ሁለት ዓመታት በኩታ ገጠም የተተከለ የሻይ ልማት ለሌሎች አካባቢዎችም ምሳሌ የሚሆን መሆኑንም ገልጸዋል። በቀጣይም የሻይ ልማት ስራው የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተጀመሩ ስራዎችን የማስፋት ስራ ይከናወናል ብለዋል።   የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ በበኩላቸው በጅማ፣ ቡኖ በደሌና ኢሉባቦር ዞኖች ባለፈው ክረምት 1 ሺህ 500 ሔክታር መሬት ላይ የተተከለው ሻይ በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ መሆኑን ተናግረዋል። ልማቱ ያለበት ሁኔታ በሻይ ልማት ኢኒሼቲቩ ላይ የነበረውን ጥርጣሬ የቀረፈ እና አርሶ አደሩም በጥሩ ተነሳሽነት ወደ ስራው እንዲገባ የሚያግዝ መሆኑንም አንስተዋል። የተተከለው ሻይ ለምርት እንዲደርስ ከመንከባከብ ጎን ለጎን የሻይ ምርት የማቀነባበሪያ ፋብሪካ የመገንባት ስራውም ቀጣይ አቅጣጫ መሆኑንም አክለዋል። ከዚሁ ጎን ለጎን የሻይ ልማቱን ለማስፋፋትም በክልሉ በሚቀጥሉት ጊዜያት የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት የተጀመረው የሻይ ልማት ስራ የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኢሉአባቦር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ ናቸው። በዚህ ወቅት ለደረሰው የሻይ ምርት የገበያ ትስስር ከመፍጠር ጎን ለጎን ቀጣይ የሚተከል ችግኝ ዝግጅት መጀመሩንም አስረድተዋል። በሀሉ ወረዳ ተደራጅተው በሻይ ልማት ስራ የተሰማሩት ወይዘሮ አበበች ደኑና አቶ ዮናስ አረጋ፣ የሻይ ምርታቸው ጥሩ ደረጃ ላይ መሆኑን ተናግረው ቀጣይ ስራውን ለማስፋፋት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
በጋምቤላ ክልል ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መታገል እንደሚገባ ተመለከተ
Dec 9, 2025 24
ጋምቤላ ፤ህዳር 30/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለዜጎች ህይወት መለወጥና ለሀገር እድገት ማነቆ የሆነውን ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መታገል እንደሚገባ ተመለከተ። ''ትውልድን በስነ-ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር እንገንባ'' በሚል መሪ ሀሳብ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በጋምቤላ ክልል ደረጃ ዛሬ በፓናል ውይይት ተከበረ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ አቶ ዶል ኡኩሪ በመድረኩ ላይ እንዳሉት እንደ ክልልም ሆነ እንደ ሀገር የልማትና የዕድገት ፀር የሆነውን ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል።   ለዜጎች ህይወት መለወጥና ለሀገር እድገት ማነቆ የሆነውን ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ በመታገል የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባልም ብለዋል። በክልሉ ህዝብንና ሀገርን በቅንነትና በታማኝነት የሚያገለግል ዜጋን ለማፍራት እየተከናወነ ያለው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም እንዲሁ። ለሌብነትና ለብልሹ አሰራር የተጋለጡ አሰራሮችን በማስተካከል እና የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር ውጤት እያስገኙ እንደሚገኝም ተወካዩ ገልፀዋል። በክልሉ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ ዜጎችን በስነ-ምግባር ማነጽና አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ደግሞ ግልጽ በሆነ አሰራር የመገንባቱ ተግባር እንደሚጠናከር ተናግረዋል።   የክልሉ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ቱት ንዑት በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የክልሉን ልማትና የህዝቦችን ተጠቃሚነት የሚጎዳ ተግባር ነው። በመሆኑም ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመታገል መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። የዛሬው የውይይት መድረክም ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ ለመከላከል ቃላችንን የምናድስበት ጭምር መሆኑንም ገልፀዋል።   በመድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።    
በጉራጌ ዞን እየተመዘገበ ያለውን የልማት ስኬት በማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትጋት እንሰራለን
Dec 9, 2025 37
ወልቂጤ፤ህዳር 30/2018 (ኢዜአ)፦በጉራጌ ዞን በመደመር መንግስት እይታ እየተመዘገበ ያለውን የልማት ስኬት በማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትጋትና በቅንጅት እንደሚሰሩ የዞኑ አመራሮች ገለጹ። የመደመር መንግሥት እይታ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በማረጋገጥና ሁለንተናዊ ለውጥ በማምጣት ህዝብን የልማቱ ተጠቃሚ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም በገጠርና በከተማ ያሉ ፀጋዎችን ለይቶ በአዲስ እይታ በማልማት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ትኩረት ስለተሰጠው ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአመራሮች ስልጠና ማጠቃለያ ላይ የመደመር መንግስትን እሳቤ ባስረዱበት ወቅት ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ለማምጣት አዲስ እይታ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በተለይም በቴክኖሎጂ የተደገፈ የግብርና ልማት ማከናወን፣ ፆም የሚያድር መሬትን ወደ ምርት መቀየር እንዲሁም የግብርና እና ገጠር ሽግግር እምርታን ማምጣት እንደሚገባም በአፅንኦት ተናግረዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የጉራጌ ዞን አመራሮችም በዞኑ ያለውን ዕምቅ ፀጋ በመደመር መንግስት እይታ ወደውጤት በመቀየር ህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትጋትና በቅንጅት እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡ ለአመራር የተሰጠው ስልጠናም በየአካባቢው የተጀመሩ የልማት ውጥኖችን በትጋትና በላቀ ተነሳሽነት ለመፈጸም አቅም እንደፈጠረላቸው ነው የተናገሩት። በብልጽግና ፓርቲ የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አለማየሁ ገብረመስቀል እንደተናገሩት፤ ስልጠናው የልማት አቅምን ለይቶ ወደ ውጤት ለመቀየር የተጀመረውን ጥረት ለማሳደግ የሚያግዝ ነው። በተለይ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚን ለማረጋገጥ፣ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እንዲሁም የከተማ ነዋሪዎችን አኗኗር ለማሻሻል የሚያስችል እውቀትና ግንዛቤ በስልጠናው እንዳገኙ ገልጸው፣ በቀጣይም ለህዝብ ተጠቃሚነት ተግተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። የሀሳብና የተግባር አንድነትን ፈጥሮ ውጤታማ ልማት በማከናወን በኩል ከዚህ ቀደም ይታዩ የነበሩ ጉድለቶችን ለማረም በትኩረት እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬታማ የልማት ስራዎችን ለማሳደግም በቅንጅትና በትጋት ለመስራት መዘጋጀታቸውንም አረጋግጠዋል። በዞኑ በግብርና ዘርፍ ያለን እምቅ አቅም ወደውጤት ለመቀየርና የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ናቸው። ለዚህም ሳይታረሱ ጾም ያድሩ የነበሩ ማሳዎችና በባህር ዛፍ የለማን ማሳ አንስቶ በተለያዩ ሰብሎች፣ አትክልት፣ ፍራፍሬና የቅመማ ቅመም ምርቶች ለመሸፈን በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ የግብርና ልማት ሥራው ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ምርጥ ዘርና የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽነት ማጠናከር፣ እንዲሁም ለኩታ ገጠም የአስተራረስ ዘዴ ትኩረት እንደሚሰጥም አቶ አበራ ተናግረዋል። ስልጠናው የብልጽግና ጉዞን ለማፋጠን የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ግብአት ያገኙበት እንደሆነ የገለጹት የዞኑ የፋይናንስ መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ ሳሊም ከድር በበኩላቸው፣ የዞኑን ልማት በማፋጠን የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል።
የሚታይ
በክልሉ ግብርናን ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች ተመዝግበዋል
Dec 9, 2025 22
አዲስ አበባ፤ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ግብርናን ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ። አቶ አወሉ አብዲ በኦሮሚያ ክልል ሸሜን ሸዋ ዞን ደብረሊባኖስ ወረዳ በኩታ ገጠም በመኸር እርሻ የለማን ስንዴ መሰበስብ አስጀምረዋል።   በዚሁ ወቅት በሰጡት ማብራሪያ በክልሉ ዘመናዊ የግብርና የእርሻ ማሽነሪዎች በመጠቀም በተሰሩ ስራዎች ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ላይ ትልቅ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። በዚህም ከተረጂነት በመላቀቅ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ እመርታ እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ ስንዴን ማምርት ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይህም የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የእርሻ ሥራ ከባለፉት ዓመታት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።   ግብዓትን ጨምሮ የሚስተዋሉ ሌሎች ማነቆዎችን በመፍታት በግብርናው ዘርፍ እመርታን ለማምጣት ያስቻሉ ስራዎች ተመዝግበዋል ብለዋል። ስንዴ ልማት ምርት በየጊዜው እየተሻሻለ እንደሚገኝ ገልፀው፤ አርሶ አደሩ የበጋ መስኖ ስንዴን በኩታ ገጠም እና በመስኖ በማልማት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአጠቃላይ የገጠር ሽግግርን በማሳለጥ የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመቀየር የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ መጠበቅ የሚያስችል የዲጂታል ሰርተፍኬት አገልግሎት ይፋ ሆነ
Dec 9, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ መጠበቅ የሚያስችል የዲጂታል ሰርተፍኬት አገልግሎትን በይፋ አስጀምሯል። አገልግሎቱ በይፋዊ ቁልፍ መሰረተ ልማት ውስጥ የፋይዳ ደህንነት ማስጠበቂያ ቁልፎች የሚፈጠሩበትና የሚንቀሳቀሱበትን አሰራር ያካተተ ነው ተብሏል።   እነዚህ ቁልፎች በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ ለመጠበቅ ጥቅም ላይ የሚውል የመተማመኛ ዲጂታል ፊርማ ለማዘጋጀት የሚውሉ መሆኑም ተገልጿል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ፤ ከዚህ ቀደም ለኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት የዲጂታል ሰርተፊኬት አገልግሎት መጀመሩን ገልጸው፤ ዛሬ በይፋ የተጀመረው የፋይዳ መታወቂያ ሰርተፊኬት አገልግሎት ቀጣይ ስራ ነው ብለዋል። የሰርተፊኬት አገልግሎቱ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በከፍተኛ የደህንነት ደረጃዎች ባላቸው ቴክኖሎጂዎች የተጠበቀ እንዲሆን ያግዛል ነው ያሉት። የማንነት ስርቆትን ለመከላከል፣ማጭበርበር እና የማንነት መረጃን አላግባብ መጠቀምን ለመከላከል የሚያስችል መሆኑንም አመልክተዋል። ደህንነቱ የተጠበቀ ዲጂታል መታወቂያ ጤና፣ ትምህርት፣ ባንክን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶች በተሻለ መልኩ ለማግኘት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው መሆኑም ነው የተገለጹት። የፋይዳን ደህንነት ማረጋገጥ ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ የተሳለጠ አገልግሎት እንዲኖር ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል።   የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያሥላሴ በበኩላቸው፤ 29 ሚሊዮን ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መመዝገባቸውን ተናግረዋል። መታወቂያ ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ደህንነቱን ማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ አኳያ የሰርተፊኬት አገልግሎቱ መጀመር ትልቅ እርምጃ ነው ብለዋል። የሰርተፊኬት አገልግሎቱ የፋይዳ ዲጂታል ሰነዶች ተዓማኒነትን የሚጨምር መሆኑንም ጠቁመዋል።
የመደመር መንግስት ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ጋራ ብልፅግና የተጀመረውን ጉዞ ለማሳካት በትጋት ይሰራል- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Dec 9, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግስት ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ጋራ ብልፅግና የተጀመረውን ጉዞ ለማሳካት፣ በመፍጠር፣ በመፍጠን እና በእመርታ መርሕ በትጋት እንደሚሰራ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዲጂታል ኢኮኖሚን መገንባት ምርጫ ሳይሆን ብልጫ ነው! በሚል ርዕስ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ሁለተኛውን የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤን በይፋ ማስጀመራቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በውጤታማነት መተግበሩ፣ ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎቶችን ተደራሽ ከማድረግ ባሻገር፣ የዕለት ከዕለት የኑሮ እንቅስቃሴን እያቀለለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተጨማሪም የኤሌክትሮኒክና የዲጂታል ግብይት ሥርዓትን ተመራጭ የክፍያ መንገድ እንዲሆን ማስቻሉን አመልክተዋል። ይሄም የሕዝብን ኑሮና የመንግሥትን አገልግሎት ከምርጫም በላይ ብልጫ ያለው እንዲሆን ያስችላል ነው ያሉት። ባለፉት አምስት ዓመታት በተዘረጋው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ውስጥ፣ በየዓመቱ ከ18.5 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ይሄንን ስኬት በላቀ መልኩ በማስቀጠል ሁሉን አቀፍ ብልፅግናን የማሳካት ግብ የያዘውን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በቅርቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁን አውስተዋል። ስትራቴጂው ዲጂታል መሠረተ ልማትን የማጠናከር፣ ተደራሽነትን ብቻ ሳይሆን አጠቃቀምን ለማስፋት ክሂሎትን የመገንባት እና ችግር ፈቺ ፈጠራን የማበረታታት ዓላማ ያለው መሆኑን ጠቅሰው ለስኬታማነቱ ሁሉም ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር መንግሥት ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ጋራ ብልፅግና የጀመርነውን ጉዞ ለማሳካት፣ በመፍጠር፣ በመፍጠን እና በእመርታ መርሕ ይተጋል ሲሉም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስና የክፍያ ሥርዓት በፈጣን የዕድገት ጎዳና ላይ ነው- የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)
Dec 9, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30፣ 2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስና የክፍያ ሥርዓት በፈጣን የዕድገት ጎዳና ላይ መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ። ከ2026 - 2030 የሚተገበረው ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ ዛሬ በሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህና ሌሎችም የመንግሥት ከፍተኛ አመራር አባላት በተገኙበት ይፋ ተደርጓል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ( ዶ/ር) በኢትዮጵያ የዲጂታል ለውጥ ከፍተኛ እድገት ላይ እንደሚገኝ በአፅንኦት ገልጸዋል። የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቶች ከፍተኛ ተቀባይነት እያገኙ እና ለኢኮኖሚ እድገት ጉልህ ሚና እያበረከቱ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ አስደናቂ የሆነ የዲጂታል ለውጥ እያስተናገደች መሆኗን ገልጸው፤ ይህም ለፋይናንስ ዘርፉ ዕድገት ትልቅ መስፈንጠሪያ እየሆነ መምጣቱን አንስተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ፈጠራን የሚያበረታቱ አሠራሮችና በዲጂታል መሠረተ ልማት ላይ እየተደረጉ ያሉ ኢንቨስትመንቶችም ለዕድገቱ ሚናቸው የላቀ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የዲጂታል ግብይቶች ፈጣን ዕድገት እያሳዩ ነው ያሉት የባንኩ ገዥ፤ ይህም በሀገሪቷ የግብይት ገጽታ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ማምጣቱን ጠቁመዋል። ይህ የዲጂታል ግብይት መጨመር፣ የዲጂታል ክፍያዎች ተቀባይነት እየጨመረ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑንም ተናግረዋል። በብሔራዊ የክፍያ መሠረተ ልማቶች ላይ እየተደረጉ ያሉ የማሻሻያ ሥራዎች ቅልጥፍናንና ደህንነትን እያሻሻሉ ሲሆን፤ ጠንካራ የዲጂታል ፋይናንስ ሥርዓት እንዲኖር መሠረት እየጣሉ ነው ብለዋል። ሰፊ የዲጂታል እምቅ አቅም ያላት ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ያለ የፋይናንስና የግብይት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን ገልጸዋል። እነዚህ ስኬቶች ቢኖሩም በቴክኖሎጂ ተደራሽነት ያሉ ክፍተቶች፣ የአጣዳፊ ጊዜ አገልግሎቶች አለመስፋት እና እያደጉ የመጡ የሳይበር ደህንነት ስጋቶችን ጨምሮ ፈተናዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። እነዚህን ፈተናዎች ለመፍታት በመንግሥት እና የግል ዘርፉ ትብብር አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የብሔራዊ ዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ (2026-2030) በፋይናንስ አገልግሎት ውስጥ አካታችነትን እንደሚያጎለብት እና ፈጠራን እንደሚያበረታታም ነው የገለጹት ገዥው። አዲሱ ስትራቴጂ አስተማማኝ እና ተዓማኒ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መዘርጋት፣ የፋይናንስ አገልግሎቶች ዲዛይን ውስጥ የፆታ አቀፍ ተጠቃሚነትን ማሳደግ እና ከድንበር ተሻጋሪ ክፍያዎች ጋር የሚጣጣም የክፍያ ስርዓትን መፍጠርን ያካትታል ብለዋል። በተጨማሪም ስትራቴጂው የብሔራዊ መረጃ ልውውጥ እንዲቋቋም እና የአስፈላጊ አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማስፋት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ጠንካራ ዲጂታል ኢኮኖሚ እየገነባች ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Dec 9, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ህዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ጠንካራ ዲጂታል ኢኮኖሚ እየገነባች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ፤ ከ2026 - 2030 የሚተገበረውን ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በተሳካ ሁኔታ በመተግበር ዘርፈ ብዙ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ተጨባጭ የዲጂታል እድገት ማስመዝገቧን ጠቅሰው፤ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት በሚያስደንቅ ፍጥነት መስፋፋቱን ተናግረዋል። መንግሥት በወሰዳቸው የሪፎርም እርምጃዎች እና የመሠረተ ልማት ግንባታ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ጠንካራ መሠረት መገንባቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ፋይናንስ ምህዳሩ በየዓመቱ ከ18 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይቶችን እያስተናገደ ነው ብለዋል። የዘርፉ ለውጥ ፈጣንና አስተማማኝ የቴሌኮምና የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማስፋት የኢኮኖሚውን ዲጂታል ጉዞ እያፋጠነ መሆኑን ገልጸዋል። የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያሉ የዲጂታል የመንግሥት አሠራሮች በመቶዎች የሚቆጠሩ አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ በማሳለጥ እንግልትን እየቀነሱና ግልጽነትን እያሻሻሉ መሆኑን ተናግረዋል። ብሔራዊ ባንክ አሠራሮችን በማዘመን ለሞባይል ገንዘብ ዝውውር፣ ለክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች እና ለፈጠራ ባለሙያዎች ምቹ ምህዳር መፍጠሩን ተናግረዋል። በኢት-ስዊች የተደገፈው ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ አሠራር ከፍተኛ ገንዘብ በባንኮች መካከል እና በዲጂታል አማራጭ በቀላሉ እንዲንቀሳቀስ አስችሏል ነው ያሉት። የቴሌብር ፈጣን ተደራሽነትና ለአጠቃቀም ምቹ መሆኑ የዕለት ተዕለት የዜጎችን ኑሮ እያሳለጠ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭን ጨምሮ ዲጂታል ክህሎትን የማጎልበት ሥራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው ተናግረዋል። በዲጂታል ዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢኮኖሚውን ወደ ፊት የሚያሻግሩ ብሔራዊ መሠረተ ልማቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ነገር ግን ከተደራሽነት ባሻገር ትርጉም ባለው አጠቃቀም ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል ነው ያሉት። የዲጂታል አጠቃቀምን ማሳደግ የአርሶና አርብቶ አደሮችን ህይወት በማሻሻል፣ ሥራቸውን በማቅለል፣ የፋይናንስ አገልግሎትን በቀላሉ እንዲያገኙ በማድረግ የአካታች ኢኮኖሚ ዕድገት ይፋጠናል ብለዋል። የዲጂታል ጉዟችን ቀጣዩ ምዕራፍ ሊለካ የሚገባው የህዝባችንን ህይወት በማሻሻል ረገድ ነው ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።   ከዚህ አኳያ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሠረተ ልማትን እንድናጠናክር፣ አጠቃቀምን ማስፋት፣ ክህሎቶችን መገንባት እና ችግሮችን የሚፈታ ፈጠራን የማበረታታት ዓላማ ያነገበ መሆኑን ገልጸዋል። ዘመኑን የዋጀው ይህ ስትራቴጂ፣ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና ማህበራዊ ዘርፎች ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ግብይት ማህበረሰቡን የሳይበር ደህንነትን በማረጋገጥ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት እና ኃላፊነት በተሞላበት አሠራር ህዝቡን ማገልገል እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በጋራ ዓላማ በማሳተፍ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚሆን ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የዲጂታል መፃኢ ዕድሏን የሚወስን ጠንካራ መሠረት አስቀድማ ገንብታለች ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በቀጣይ ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ተፅዕኖ እና ወደ ጋራ ብልጽግና የሚደረገውን ሽግግር ማፋጠን እንደሚገባ ጠቁመዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በሐረሪ ክልል የሰላምና ፀጥታ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር
Dec 9, 2025 36
ጅግጅጋ ፤ህዳር 30/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል የሰላምና ፀጥታ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር ተናገሩ። የምስራቅ እዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ የሐረሪ ክልል የፀጥታ አካላት ዛሬ ተመርቀዋል።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር በምረቃው ላይ ተገኝተው እንዳሉት በክልሉ ሰላምና ፀጥታን የማጠናከር ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል። ለዚህም የፀጥታ ሃይሉ ህዝቡና የሰላም አደረጃጀቶች የሚያከናውኑት የተቀናጀ ስራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። ልማትና እድገትን ይበልጥ ለማጎልበትና ሰላምን ለማጽናት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ወይዘሮ ሮዛ አመልክተዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ የሀገርን ሰላምና የህዝቦችን ደህንነት የማስጠበቅ ተልዕኮውን በትጋት እየተወጣ ነው ያሉት ደግሞ የእዙ ምክትል አዛዥ ሜጄር ጄነራል ፍቃዱ ፀጋዬ ናቸው።   በተለይም እዙ በቀጠናው ፀጥታና ልማትን ጨምሮ በሁሉም ዘርፎች የሚያከናውነው ስራ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። እዙ በቀጠናው እያከናወነ የሚገኘው ስራ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ ለክልሉ ፀጥታ ሃይል ስልጠና በመስጠት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡት ደግሞ የሐረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ አቶ ተውፊቅ መሀመድ ናቸው።   ስልጠናው የክልሉ የፀጥታ አካላት የተሻለ ብቃት እንዲላበሱና እና ወታደራዊ ዝግጁነት እንዲያጎለብቱ የሚያስችል መሆኑንም አስረድተዋል። በመርሃ- ግብሩ ላይ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች፣ የሐረሪና የሶማሌ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።  
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም ይካሄዳል
Dec 9, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30፣ 2018(ኢዜአ)፦የዘንድሮው ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ2018 ዓ.ም ለሚያከናውነው 7ኛው አገራዊ ምርጫ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ቦርዱ እስካሁን በሰራቸው የቅድመ-ምርጫ ሥራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። በዚህም ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች ሲሰሩ ቆይቷል ብለዋል። ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችን የማደራጀት እንዲሁም የምርጫ ጣቢያዎች ምቹ መሆን የማረጋገጥ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውን ለህዝቡ የሚያስተዋውቁበት ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመዋል። የእጩዎች ምዝገባ ቦርዱ ባለማው ሶፍትዌር አማካኝነት እንደሚካሄድ ገልጸዋል። ለዚህም ፓርቲዎች ወይም በግል የሚወዳደሩ ራሳቸውን የመመዝገብ ስራ እንደሚሰሩ ገልጸው፤ ለዚህም ቦርዱ ስልጠና መስጠቱን አመልክተዋል። እንዲሁም መራጮችም በቦርዱ በለማው ሶፍትዌር እና ከዚህ ቀደም ባለው አሰራር በማኑዋል ምዝገባ እንደሚያካሂዱ ተናግረዋል። መራጮች ለምዝገባ የሚያቀርቡት መረጃም እንደቀድሞው የሚቀጥል መሆኑን አስታውቀዋል። የታዛቢ ፈቃድ ለጠየቁም ቦርዱ ባለማው ሶፍትዌር አማካኝነት ፈቃድ ለመስጠት በመጨረሻ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ተናግረው፤ ግንቦት 24 ቀን 2018 የድምጽ መስጫ ቀን መሆኑን ጠቁመዋል። አስቻይ ሁኔታዎችን በተመለከተ ቀጣይነት ያላቸው ውይይቶች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚደረጉ ተናግረዋል።
አዲሃን ለሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የድርሻውን እንደሚወጣ ገለጸ
Dec 8, 2025 168
ባሕር ዳር፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ንቅናቄ (አዲሃን) ለሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የድርሻውን የሚወጣ መሆኑን ገለጸ። የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ንቅናቄ (አዲሃን) ለሁለት ቀናት ያካሄደውን 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ማጠናቀቁን ተከትሎ የንቅናቄው የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ ራስወርቅ መላኩ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ፓርቲው በሰላማዊ ትግል ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው ለሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የድርሻውን የሚወጣ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የፓርቲው የጥናትና ምርምር ሃላፊ አዲሱ ጉልላት (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጠናከር እንዲሁም ለሰላምና የልማት ስራዎች የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል። በጉባኤው የአመራሮችን ምርጫ በማካሄድ ፓርቲውን አቶ ተስፋሁን አለምነህ በሊቀመንበርነት እንዲሁም አዳነ ወዳጀነህ (ዶ/ር) በምክትል ሊቀመንበርነት እንዲመሩ መርጧል። በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋህድ) መካከል ዘላቂ የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ የኃይል አማራጭ ተቀባይነት እንደሌለው ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ተስፋሁን አለምነህ መግለፃቸው ይታወሳል።
20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በውጭ በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ተከበረ
Dec 8, 2025 169
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች ተከብሯል። በዓሉ የተከበረው "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ነው። በአከባበሩ ላይ የሚሲዮን መሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና ሰራተኞች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የማህበረሰብ ተወካዮችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ኢትዮጵያ የብዝኃነት ተምሳሌት እና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ባሳየ መልኩ ተከብሯል። የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦችና አልባሳት ለእይታ የቀረቡ ሲሆን የብሔሮች ብሔረሰቦች ሙዚቃዎችና ባሕላዊ ውዝዋዜዎች የሚገልጹ ሁነቶችም ቀርበዋል። በዓሉ በቻይና፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ቱርኪዬ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኳታር፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቤልጂየም፣ ፓኪስታን፣ ኮትዲቭዋር፣ ስዊድን፣ ኮሪያ ሪፐብሊክ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ አውስትራሊያ፣ ዩጋንዳ፣ ሩዋንዳ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ ቀኑ ከተከበረባቸው ሀገራት መካከል ይገኙበታል። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ዛሬ ተከብሯል።
ብልጽግና ፓርቲ ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ
Dec 8, 2025 140
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ብልጽግና ፓርቲ ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ፓርቲው ያስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡- እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አደረሰን አደረሳችሁ! የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በየደረጃውና በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር ቆይቶ በዛሬው ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በደማቅ የማጠቃለያ መርሀግብር እየተገባደደ ይገኛል፡፡ የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ከህዳር 01 ጀምሮ ለተከታታይ አንድ ወር በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በደማቅ ኩነት እንዲከበር ተደርጓል፡፡ ይህም እውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት እና ፌዴራላዊ ሥርዓት ለመገንባት የተያዘው ቁርጠኝነት ማሳያ ነው፡፡   ብልፅግና ፓርቲና የመደመር መንግሥት 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ከዕለታዊ ክብረበዓል በላይ የአጀንዳው ትክክለኛ አስፈላጊነት በውል በመረዳት በበዓሉ ስያሜ የተገለጹትን የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የፍትህ፣ የእኩልነት፣ የልማትና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች በተግባር በመመለስ መሆን አለበት ብሎ ያምናል፡፡ ለዚህም በዓሉ በአንድ ቀን ከማክበር አንድ ወር ሙሉ በመውሰድ በየክልሉና ከተማ አስተዳደሩ ያሉት ባህሎችና ነባራዊ እውነታዎች ታሳቢ በማድረግ በተከታታይ እንዲከበር መደረጉ የዚህ እምነት አንዱ ማሳያ ነው፡፡ በዓሉ “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል እንዲከበር የተመረጠበት ምክንያት እውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት እና ፌዴራላዊ ሥርዓት የሚገነባው ዴሞክራሲያዊ መግባባት በመፍጠር መሆኑ በግልጽ አመላክቷል፡፡ ዴሞክራሲያዊ መግባባት ወይም የመግባባት ዴሞክራሲ የሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት ከሆኑ ዕሳቤዎችና ተግባራት አንዱ ሲሆን የሀገራችን የዘመናት ችግር እና የሥርዓት ስብራት ሆኖ የቆየውን የዴሞክራሲ ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ እየተተገበረ ያለ ዕሳቤ ነው፡፡ ዋነኛው የኢትዮጵያ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ጥያቄ የዴሞክራሲ ጥያቄ ነበረ፡፡ ከለውጡ በፊት በነበሩት ዓመታት ይህንን በዓል የዕሳቤ ጥራት እና የተግባር ቁርጠኝነት ያልተፈጠረበት የይስሙላ የአደባባይ ትዕይንት ሆኖ ሲከበር ቆይቷል፡፡ ሙሉ ዕይታን መለያው ያደረገው ብልፅግና ፓርቲ ይህንን የዕይታና የተግባር ክፍተት በማረቅ የጎደሉትን የእውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት፣ ፌዴራላዊ ሥርዓት እና ዴሞክራሲያዊ መግባባት አላባውያን በማገናኘት ወደ ተቃና የለወጥና የዝላይ ምዕራፍ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ዴሞክራሲያዊ መግባባት የተዋንያን በተለይ ደግሞ የህዝብ ይሁንታና ተሳትፎ የሚያስተናግድ ዕሳቤና ማህበራዊ ውል ነው፡፡ የዴሞክራሲያዊ መግባባት አንዱና ዋነኛ መገለጫ ምርጫ ሲሆን የዘንድሮው የህዳር 29 በዓል ከ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ጋር ተያይዞ የሚታይ ነው፡፡ ያለፈው 6ኛ ሀገራዊ ምርጫ ለዴሞክራሲያዊ መግባባት መሠረት የጣለ ስኬታማ ምርጫ እንደነበረው ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ደግሞ የዚህ ዕሳቤና ማህበራዊ ውል የአፈጻጸም ከፍታ የሚታይበት እንዲሆን አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡ በዓሉ በያዝነው ዓመት ሲከበር የኢትዮጵያ ብልፅግና አይቀሬ ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ ፕሮጀክት መሆኑ በአያሌ ማሳያዎች የተረጋገጠበት በመሆኑ በዓሉ ይበልጥ ደማቅ አድርጎታል፡፡ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ መመረቅ ብልፅግና ፓርቲ ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር እንደሚፈጸም ማሳያ ነው፡፡ በዕለቱ የተበሰሩ 7ቱ በጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች ሆነው የዚህ ተግባር ቀጣይነት በማሳየት በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ መተማመንና ቅቡልነት ለመፍጠር ተችሎበታል፡፡ ይህ በመፍጠን፣ መፍጠርና ዝላይ የታጀበ አስደናቂ የልማት አርበኝነት የባህር በር አጀንዳችን ላይ ለመድገም ስንቅ በመሆን “ከግድቡ ወደ ባህሩ” በሚል ህዝባዊ መፈክር ከታሪካችንና ከማንነታችን አለአግባብ የተወሰደብንን የባህር በር ጥያቄያችን በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለማስመለስ እንደ ህዝብና ሀገር አንድ ሆነን እየሰራንበት እንገኛለን፡፡ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ስናከብር የመደመር መንግሥት ያስቀመጣቸውን አሻጋሪና ተስተካካይ ዕቅዶች እየተተገበሩና ውጤት እያመጡ መሆናቸውና ለዚህም ህዝብ በባለቤትነት የሚሳተፍበትና ተጠቃሚ እየሆነበት ያለ መሆኑ በመገንዘብ ነው፡፡ በቀጣይ ዓመት 21ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የምናከብረውም በአንድ እጃችን የጀመርናቸው የፀጥታና የልማት ሥራዎች አሳክተን በሌላው እጃችን ደግሞ ህዝቦች ለዘመናት የታገሉለትን የዴሞክራሲ ሥርአት ወደ ላቀ ደረጃ አድርሰን ነው፡፡ በጉጉት የሚጠበቀውና ነጻ፣ ፍትሀዊና አሳታፊ በመሆን የዴሞክራሲ እመርታ እንዲፈጠርበት በሚጠበቀው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች እንደ ከዚህ ቀደሙ በባለቤትነትና በላቀ ተነሳሽነት በመሳተፍ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሀገራችን ፀጥታ፣ ልማትና ዴሞክራሲ የሚጎመዝዛቸው ባዳዎችና ባንዳዎች ሀገር አፍራሽ እንቅስቃሴዎቻቸውን በንቃት በመከታተልና በመመከት እንዲሁም በዛሬው ቀን በድምቀት እያጠቃለልነው ያለነው በዓል መሪ ቃል የሆነውን “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” ተግባራዊ ለማድረግ ዴሞክራሲያዊ መግባባታችንን እና ህብረብሄራዊ አንድነታችንን በማጽናት መሆን አለበት፡፡ መልካም 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል! ብልፅግና ፓርቲ ህዳር 29፤ 2018 ዓ.ም
ፖለቲካ
በሐረሪ ክልል የሰላምና ፀጥታ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር
Dec 9, 2025 36
ጅግጅጋ ፤ህዳር 30/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል የሰላምና ፀጥታ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር ተናገሩ። የምስራቅ እዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ የሐረሪ ክልል የፀጥታ አካላት ዛሬ ተመርቀዋል።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር በምረቃው ላይ ተገኝተው እንዳሉት በክልሉ ሰላምና ፀጥታን የማጠናከር ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል። ለዚህም የፀጥታ ሃይሉ ህዝቡና የሰላም አደረጃጀቶች የሚያከናውኑት የተቀናጀ ስራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። ልማትና እድገትን ይበልጥ ለማጎልበትና ሰላምን ለማጽናት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ወይዘሮ ሮዛ አመልክተዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ የሀገርን ሰላምና የህዝቦችን ደህንነት የማስጠበቅ ተልዕኮውን በትጋት እየተወጣ ነው ያሉት ደግሞ የእዙ ምክትል አዛዥ ሜጄር ጄነራል ፍቃዱ ፀጋዬ ናቸው።   በተለይም እዙ በቀጠናው ፀጥታና ልማትን ጨምሮ በሁሉም ዘርፎች የሚያከናውነው ስራ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። እዙ በቀጠናው እያከናወነ የሚገኘው ስራ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ ለክልሉ ፀጥታ ሃይል ስልጠና በመስጠት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡት ደግሞ የሐረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ አቶ ተውፊቅ መሀመድ ናቸው።   ስልጠናው የክልሉ የፀጥታ አካላት የተሻለ ብቃት እንዲላበሱና እና ወታደራዊ ዝግጁነት እንዲያጎለብቱ የሚያስችል መሆኑንም አስረድተዋል። በመርሃ- ግብሩ ላይ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች፣ የሐረሪና የሶማሌ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።  
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም ይካሄዳል
Dec 9, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30፣ 2018(ኢዜአ)፦የዘንድሮው ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ2018 ዓ.ም ለሚያከናውነው 7ኛው አገራዊ ምርጫ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ቦርዱ እስካሁን በሰራቸው የቅድመ-ምርጫ ሥራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። በዚህም ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች ሲሰሩ ቆይቷል ብለዋል። ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችን የማደራጀት እንዲሁም የምርጫ ጣቢያዎች ምቹ መሆን የማረጋገጥ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውን ለህዝቡ የሚያስተዋውቁበት ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመዋል። የእጩዎች ምዝገባ ቦርዱ ባለማው ሶፍትዌር አማካኝነት እንደሚካሄድ ገልጸዋል። ለዚህም ፓርቲዎች ወይም በግል የሚወዳደሩ ራሳቸውን የመመዝገብ ስራ እንደሚሰሩ ገልጸው፤ ለዚህም ቦርዱ ስልጠና መስጠቱን አመልክተዋል። እንዲሁም መራጮችም በቦርዱ በለማው ሶፍትዌር እና ከዚህ ቀደም ባለው አሰራር በማኑዋል ምዝገባ እንደሚያካሂዱ ተናግረዋል። መራጮች ለምዝገባ የሚያቀርቡት መረጃም እንደቀድሞው የሚቀጥል መሆኑን አስታውቀዋል። የታዛቢ ፈቃድ ለጠየቁም ቦርዱ ባለማው ሶፍትዌር አማካኝነት ፈቃድ ለመስጠት በመጨረሻ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ተናግረው፤ ግንቦት 24 ቀን 2018 የድምጽ መስጫ ቀን መሆኑን ጠቁመዋል። አስቻይ ሁኔታዎችን በተመለከተ ቀጣይነት ያላቸው ውይይቶች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚደረጉ ተናግረዋል።
አዲሃን ለሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የድርሻውን እንደሚወጣ ገለጸ
Dec 8, 2025 168
ባሕር ዳር፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ንቅናቄ (አዲሃን) ለሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የድርሻውን የሚወጣ መሆኑን ገለጸ። የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ንቅናቄ (አዲሃን) ለሁለት ቀናት ያካሄደውን 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ማጠናቀቁን ተከትሎ የንቅናቄው የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ ራስወርቅ መላኩ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ፓርቲው በሰላማዊ ትግል ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው ለሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የድርሻውን የሚወጣ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የፓርቲው የጥናትና ምርምር ሃላፊ አዲሱ ጉልላት (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጠናከር እንዲሁም ለሰላምና የልማት ስራዎች የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል። በጉባኤው የአመራሮችን ምርጫ በማካሄድ ፓርቲውን አቶ ተስፋሁን አለምነህ በሊቀመንበርነት እንዲሁም አዳነ ወዳጀነህ (ዶ/ር) በምክትል ሊቀመንበርነት እንዲመሩ መርጧል። በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋህድ) መካከል ዘላቂ የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ የኃይል አማራጭ ተቀባይነት እንደሌለው ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ተስፋሁን አለምነህ መግለፃቸው ይታወሳል።
20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በውጭ በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ተከበረ
Dec 8, 2025 169
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች ተከብሯል። በዓሉ የተከበረው "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ነው። በአከባበሩ ላይ የሚሲዮን መሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና ሰራተኞች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የማህበረሰብ ተወካዮችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ኢትዮጵያ የብዝኃነት ተምሳሌት እና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ባሳየ መልኩ ተከብሯል። የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦችና አልባሳት ለእይታ የቀረቡ ሲሆን የብሔሮች ብሔረሰቦች ሙዚቃዎችና ባሕላዊ ውዝዋዜዎች የሚገልጹ ሁነቶችም ቀርበዋል። በዓሉ በቻይና፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ቱርኪዬ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኳታር፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቤልጂየም፣ ፓኪስታን፣ ኮትዲቭዋር፣ ስዊድን፣ ኮሪያ ሪፐብሊክ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ አውስትራሊያ፣ ዩጋንዳ፣ ሩዋንዳ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ ቀኑ ከተከበረባቸው ሀገራት መካከል ይገኙበታል። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ዛሬ ተከብሯል።
ብልጽግና ፓርቲ ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ
Dec 8, 2025 140
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ብልጽግና ፓርቲ ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ፓርቲው ያስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡- እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አደረሰን አደረሳችሁ! የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በየደረጃውና በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር ቆይቶ በዛሬው ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በደማቅ የማጠቃለያ መርሀግብር እየተገባደደ ይገኛል፡፡ የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ከህዳር 01 ጀምሮ ለተከታታይ አንድ ወር በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በደማቅ ኩነት እንዲከበር ተደርጓል፡፡ ይህም እውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት እና ፌዴራላዊ ሥርዓት ለመገንባት የተያዘው ቁርጠኝነት ማሳያ ነው፡፡   ብልፅግና ፓርቲና የመደመር መንግሥት 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ከዕለታዊ ክብረበዓል በላይ የአጀንዳው ትክክለኛ አስፈላጊነት በውል በመረዳት በበዓሉ ስያሜ የተገለጹትን የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የፍትህ፣ የእኩልነት፣ የልማትና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች በተግባር በመመለስ መሆን አለበት ብሎ ያምናል፡፡ ለዚህም በዓሉ በአንድ ቀን ከማክበር አንድ ወር ሙሉ በመውሰድ በየክልሉና ከተማ አስተዳደሩ ያሉት ባህሎችና ነባራዊ እውነታዎች ታሳቢ በማድረግ በተከታታይ እንዲከበር መደረጉ የዚህ እምነት አንዱ ማሳያ ነው፡፡ በዓሉ “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል እንዲከበር የተመረጠበት ምክንያት እውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት እና ፌዴራላዊ ሥርዓት የሚገነባው ዴሞክራሲያዊ መግባባት በመፍጠር መሆኑ በግልጽ አመላክቷል፡፡ ዴሞክራሲያዊ መግባባት ወይም የመግባባት ዴሞክራሲ የሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት ከሆኑ ዕሳቤዎችና ተግባራት አንዱ ሲሆን የሀገራችን የዘመናት ችግር እና የሥርዓት ስብራት ሆኖ የቆየውን የዴሞክራሲ ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ እየተተገበረ ያለ ዕሳቤ ነው፡፡ ዋነኛው የኢትዮጵያ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ጥያቄ የዴሞክራሲ ጥያቄ ነበረ፡፡ ከለውጡ በፊት በነበሩት ዓመታት ይህንን በዓል የዕሳቤ ጥራት እና የተግባር ቁርጠኝነት ያልተፈጠረበት የይስሙላ የአደባባይ ትዕይንት ሆኖ ሲከበር ቆይቷል፡፡ ሙሉ ዕይታን መለያው ያደረገው ብልፅግና ፓርቲ ይህንን የዕይታና የተግባር ክፍተት በማረቅ የጎደሉትን የእውነተኛ ህብረብሄራዊ አንድነት፣ ፌዴራላዊ ሥርዓት እና ዴሞክራሲያዊ መግባባት አላባውያን በማገናኘት ወደ ተቃና የለወጥና የዝላይ ምዕራፍ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ዴሞክራሲያዊ መግባባት የተዋንያን በተለይ ደግሞ የህዝብ ይሁንታና ተሳትፎ የሚያስተናግድ ዕሳቤና ማህበራዊ ውል ነው፡፡ የዴሞክራሲያዊ መግባባት አንዱና ዋነኛ መገለጫ ምርጫ ሲሆን የዘንድሮው የህዳር 29 በዓል ከ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ጋር ተያይዞ የሚታይ ነው፡፡ ያለፈው 6ኛ ሀገራዊ ምርጫ ለዴሞክራሲያዊ መግባባት መሠረት የጣለ ስኬታማ ምርጫ እንደነበረው ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ደግሞ የዚህ ዕሳቤና ማህበራዊ ውል የአፈጻጸም ከፍታ የሚታይበት እንዲሆን አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡ በዓሉ በያዝነው ዓመት ሲከበር የኢትዮጵያ ብልፅግና አይቀሬ ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ ፕሮጀክት መሆኑ በአያሌ ማሳያዎች የተረጋገጠበት በመሆኑ በዓሉ ይበልጥ ደማቅ አድርጎታል፡፡ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ መመረቅ ብልፅግና ፓርቲ ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር እንደሚፈጸም ማሳያ ነው፡፡ በዕለቱ የተበሰሩ 7ቱ በጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች ሆነው የዚህ ተግባር ቀጣይነት በማሳየት በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ መተማመንና ቅቡልነት ለመፍጠር ተችሎበታል፡፡ ይህ በመፍጠን፣ መፍጠርና ዝላይ የታጀበ አስደናቂ የልማት አርበኝነት የባህር በር አጀንዳችን ላይ ለመድገም ስንቅ በመሆን “ከግድቡ ወደ ባህሩ” በሚል ህዝባዊ መፈክር ከታሪካችንና ከማንነታችን አለአግባብ የተወሰደብንን የባህር በር ጥያቄያችን በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለማስመለስ እንደ ህዝብና ሀገር አንድ ሆነን እየሰራንበት እንገኛለን፡፡ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ስናከብር የመደመር መንግሥት ያስቀመጣቸውን አሻጋሪና ተስተካካይ ዕቅዶች እየተተገበሩና ውጤት እያመጡ መሆናቸውና ለዚህም ህዝብ በባለቤትነት የሚሳተፍበትና ተጠቃሚ እየሆነበት ያለ መሆኑ በመገንዘብ ነው፡፡ በቀጣይ ዓመት 21ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የምናከብረውም በአንድ እጃችን የጀመርናቸው የፀጥታና የልማት ሥራዎች አሳክተን በሌላው እጃችን ደግሞ ህዝቦች ለዘመናት የታገሉለትን የዴሞክራሲ ሥርአት ወደ ላቀ ደረጃ አድርሰን ነው፡፡ በጉጉት የሚጠበቀውና ነጻ፣ ፍትሀዊና አሳታፊ በመሆን የዴሞክራሲ እመርታ እንዲፈጠርበት በሚጠበቀው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች እንደ ከዚህ ቀደሙ በባለቤትነትና በላቀ ተነሳሽነት በመሳተፍ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሀገራችን ፀጥታ፣ ልማትና ዴሞክራሲ የሚጎመዝዛቸው ባዳዎችና ባንዳዎች ሀገር አፍራሽ እንቅስቃሴዎቻቸውን በንቃት በመከታተልና በመመከት እንዲሁም በዛሬው ቀን በድምቀት እያጠቃለልነው ያለነው በዓል መሪ ቃል የሆነውን “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት” ተግባራዊ ለማድረግ ዴሞክራሲያዊ መግባባታችንን እና ህብረብሄራዊ አንድነታችንን በማጽናት መሆን አለበት፡፡ መልካም 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል! ብልፅግና ፓርቲ ህዳር 29፤ 2018 ዓ.ም
ማህበራዊ
በጋምቤላ ክልል ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መታገል እንደሚገባ ተመለከተ
Dec 9, 2025 24
ጋምቤላ ፤ህዳር 30/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለዜጎች ህይወት መለወጥና ለሀገር እድገት ማነቆ የሆነውን ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መታገል እንደሚገባ ተመለከተ። ''ትውልድን በስነ-ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር እንገንባ'' በሚል መሪ ሀሳብ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በጋምቤላ ክልል ደረጃ ዛሬ በፓናል ውይይት ተከበረ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ አቶ ዶል ኡኩሪ በመድረኩ ላይ እንዳሉት እንደ ክልልም ሆነ እንደ ሀገር የልማትና የዕድገት ፀር የሆነውን ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል።   ለዜጎች ህይወት መለወጥና ለሀገር እድገት ማነቆ የሆነውን ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ በመታገል የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባልም ብለዋል። በክልሉ ህዝብንና ሀገርን በቅንነትና በታማኝነት የሚያገለግል ዜጋን ለማፍራት እየተከናወነ ያለው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም እንዲሁ። ለሌብነትና ለብልሹ አሰራር የተጋለጡ አሰራሮችን በማስተካከል እና የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር ውጤት እያስገኙ እንደሚገኝም ተወካዩ ገልፀዋል። በክልሉ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ ዜጎችን በስነ-ምግባር ማነጽና አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ደግሞ ግልጽ በሆነ አሰራር የመገንባቱ ተግባር እንደሚጠናከር ተናግረዋል።   የክልሉ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ቱት ንዑት በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የክልሉን ልማትና የህዝቦችን ተጠቃሚነት የሚጎዳ ተግባር ነው። በመሆኑም ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመታገል መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። የዛሬው የውይይት መድረክም ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ ለመከላከል ቃላችንን የምናድስበት ጭምር መሆኑንም ገልፀዋል።   በመድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።    
በዓሉ የኢትዮጵያን መልክ ያየንበትና የደመቀ ነው -የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ተሳታፊዎች
Dec 8, 2025 122
ሆሳዕና ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የኢትዮጵያን ትክክለኛ መልክ ያየንበትና የደመቀ ነው ሲሉ የበዓሉ ተሳታፊዎች ተናገሩ። 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ተከብሯል። ከተለያዩ አካባቢዎች በመምጣት በበዓሉ የታደሙ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል የኢትዮጵያን ትክክለኛ መልክ ያዩበትና በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል። ከትግራይ ክልል የመጣችው ወጣት ራሄል ገብረሚካኤል በሰጠችው አስተያየት እኛ ኢትዮጵያውያን በአብሮነትና በትብብር ስንጓዝ የተለየ ውበት እንዳለን በበዓሉ አከባበር ላይ ተመልክቻለሁ ብላለች። በዓሉን ኢትዮጵያን በሚገልጹ የተለያዩ ማንነቶች በደመቀና ባማረ መልኩ ማክበራቸውን የተናገሩት ደግሞ ከሲዳማ ክልል የተሳተፉት አቶ አስናቀ አየለ ናቸው፡፡ በዓሉ ባህልና ትውፊቶችን ለመለዋወጥ ዕድል ከመፍጠሩ ባሻገር የአብሮነት እሴቶች እንዲጠናከሩ ሚናው የማይተካ ነው ብለዋል። ከአፋር ክልል በቀኑ አከባበር ላይ የተሳተፈው ወጣት አሊሚራሀ አህመድ በበኩሉ በሆሳዕና ከተማ የበዓሉ አከባበር የተለየ መሆኑን አንስቶ፤ ከእንግዳ አቀባበል ጀምሮ የአብሮነትና ኢትዮጵያዊነት እሴት የተንፀባረቀበት በመሆኑ መደሰቱን ገልጿል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የተጀመረውን ሁለንተናዊ የለውጥ እንቅስቃሴ ለማጠናከር እንዲህ ያሉ ህብረ-ብሔራዊ በዓላት አበርክቷቸው የጎላ መሆኑንም ነው የተናገረው፡፡ "የብሔር ብሔረሰቦች በዓል ከውበትነት ባለፈ አብሮነትን በማጠናከር ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በማጠናቀቅ ሀገር ለመለወጥ አቅም እየሆነ መጥቷል" ሲሉ የተናገሩት ደግሞ ከስልጤ ዞን የታደሙት ይርዳው ናስር (ዶ/ር)ናቸው፡፡ በዓሉ አብሮነትን ከማጠናከር በተጨማሪ ለሀገረ መንግሥት ግንባታው መጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልፀዋል፡፡
ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ይካሄዳል-ኢንስቲትዩቱ
Dec 8, 2025 198
አዳማ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ )፡- ሀገር አቀፍ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የክትባት ዘመቻውን ለማሳካት ያለመ የባለድርሻ አካላት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።   በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች ቅኝትና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክተሩ ተወካይ አቶ እንዳለ ዘመነ እንደገለጹት፤ ፖሊዮን ለማጥፋት የተቀናጀ ሀገር አቀፍ ክትባት ዘመቻ በመላው ሀገሪቱ ይካሄዳል። ዘመቻውን ስኬታማ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የክትባት ዘመቻው 25 ሚሊዮን የሚሆኑ ሕፃናት ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በሁሉም ክልሎች የክትባቱ ቁሳቁስና ተያያዥ ግብዓት አቅርቦት በየወረዳዎቹ የጤና ተቋማት ደርሰው ወደ ቀበሌዎች እየተሰራጩ እንደሚገኙ አንስተው፤ የሰው ሃይል ዝግጅትን ጨምሮ የሕብረተሰብ ንቅናቄ መካሄዱንም አክለዋል።   በዘመቻው የቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት ከመስጠት ጎን ለጎን የበሽታው ምልክት ያሳዩትን ሕፃናት የመለየት ስራ እንደሚከናወን አስረድተዋል። በጤና ሚኒስቴር የክትባት ፕሮግራም የኮሙኒኬሽን አማካሪ ወይዘሮ ፀጋነሽ ገድሉ እንዳመለከቱት፤ በዘመቻው መደበኛ የፖሊዮ ክትባት ያልወሰዱ ሕፃናት ይካተቱበታል። በጊዜያዊ የክትባት ጣቢያዎችና ወደ ጤና ተቋማት ሄደው ክትባቱን እንዲወስዱ የማድረግ ስራ ይሰራል ነው ያሉት ።   ክትባቱ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ከተሞች፤ ወረዳዎችና ቀበሌዎች በተመሳሳይ ወቅት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ ለስኬታማነቱም በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ትብብርና ዕገዛ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል ።  
የመደመር መንግሥት እይታ በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር ፈጥሯል
Dec 8, 2025 128
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት እይታ በኦሮሚያ ክልል ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር መፍጠሩን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። የዓለም ቱሪዝም ቀን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ለ21ኛጊዜ “ቱሪዝምና ዘላቂ ለውጥ” በሚል መሪ ሃሳብ በክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አዘጋጅነት በምሥራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ከተማ ተከብሯል።   የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን ታምሩ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሀብቶች ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ተደርጓል። የመደመር መንግሥት እይታ በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሃብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ምቹ ምህዳር መፍጠሩን ገልጸው፤በክልሉ ያሉ ሁሉም ወረዳዎች የራሳቸው የቱሪዝም መዳረሻ እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት። የምስራቅ ባሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጃርሶ ቦሩና በበኩላቸው ዞኑ በርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ሃብቶች እንዳሉት ተናግረዋል።   ለአብነትም የሶፍ ዑመር ዋሻ፣ ድሬ ሼህ ሁሴን፣ አስደናቂ መልክዓ ምድሮች እና ጥቅጥቅ አረንጓዴ አካባቢዎች እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። ከዚህ ቀደም በአካባቢው የሚገኙትን ሃብቶች በማልማት ረገድ ምንም እንዳልተሰራ አንስተው፤ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በፌዴራልና በክልሉ መንግሥት ሰፋፊ መሠረተ ልማቶች በትኩረት እየተገነቡ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ የመንገድ፣ የመብራት፣ የቴሌኮም ኔትወርክን ጨምሮ ቱሪዝምን የሚያነቃቁ መሠረተ ልማቶች በመገንባታቸው ዞኑ ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆን መቻሉን ተናግረዋል። መሠረተ ልማቶቹ በዞኑ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ ማገዛቸውን አስታውቀዋል።  
ኢኮኖሚ
በክልሉ ግብርናን ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች ተመዝግበዋል
Dec 9, 2025 22
አዲስ አበባ፤ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ግብርናን ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ። አቶ አወሉ አብዲ በኦሮሚያ ክልል ሸሜን ሸዋ ዞን ደብረሊባኖስ ወረዳ በኩታ ገጠም በመኸር እርሻ የለማን ስንዴ መሰበስብ አስጀምረዋል።   በዚሁ ወቅት በሰጡት ማብራሪያ በክልሉ ዘመናዊ የግብርና የእርሻ ማሽነሪዎች በመጠቀም በተሰሩ ስራዎች ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ላይ ትልቅ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። በዚህም ከተረጂነት በመላቀቅ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ እመርታ እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ ስንዴን ማምርት ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይህም የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የእርሻ ሥራ ከባለፉት ዓመታት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።   ግብዓትን ጨምሮ የሚስተዋሉ ሌሎች ማነቆዎችን በመፍታት በግብርናው ዘርፍ እመርታን ለማምጣት ያስቻሉ ስራዎች ተመዝግበዋል ብለዋል። ስንዴ ልማት ምርት በየጊዜው እየተሻሻለ እንደሚገኝ ገልፀው፤ አርሶ አደሩ የበጋ መስኖ ስንዴን በኩታ ገጠም እና በመስኖ በማልማት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአጠቃላይ የገጠር ሽግግርን በማሳለጥ የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመቀየር የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በዞኖቹ እየተተገበረ የሚገኘው የሻይ ልማት ኢኒሼቲቭ ለገጠሩ ማሕበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ተስፋ የሚጣልበት ነው
Dec 9, 2025 19
መቱ ፤ሕዳር 30/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በጅማ፣ ቡኖ በደሌና ኢሉአባቦር ዞኖች እየተተገበረ የሚገኘው የሻይ ልማት ኢኒሼቲቭ ለገጠሩ ማሕበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ተስፋ የሚጣልበት መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ ተናገሩ። በዞኖቹ ባለፉት ሁለት ዓመታት የተተከሉት የሻይ ችግኞች በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን በማንሳት በመጪው ክረምት የሚተከል የሻይ ችግኝ ዝግጅት ከወዲሁ መጀመሩን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ናቸው።   በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ መንግስት የስራ ሀላፊዎች በኢሉባቦር ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የተለያዩ የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ነው። አቶ ነመራ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በምዕራብ ኦሮሚያ ሶስት ዞኖች እየተተገበረ የሚገኘው የሻይ ልማት ተስፋ ሰጪ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተለይም በጅማ፣ ቡኖ በደሌ እና ኢሉ አባቦር ዞኖች በኢኒሼቲቭ መልክ እየተገበረ የሚገኘው የሻይ ልማት ለገጠሩ ማሕበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ተስፋ የሚጣልበት ነው ብለዋል። በኢሉአባቦር ዞን በሀሉ ወረዳ ባለፉት ሁለት ዓመታት በኩታ ገጠም የተተከለ የሻይ ልማት ለሌሎች አካባቢዎችም ምሳሌ የሚሆን መሆኑንም ገልጸዋል። በቀጣይም የሻይ ልማት ስራው የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተጀመሩ ስራዎችን የማስፋት ስራ ይከናወናል ብለዋል።   የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ በበኩላቸው በጅማ፣ ቡኖ በደሌና ኢሉባቦር ዞኖች ባለፈው ክረምት 1 ሺህ 500 ሔክታር መሬት ላይ የተተከለው ሻይ በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ መሆኑን ተናግረዋል። ልማቱ ያለበት ሁኔታ በሻይ ልማት ኢኒሼቲቩ ላይ የነበረውን ጥርጣሬ የቀረፈ እና አርሶ አደሩም በጥሩ ተነሳሽነት ወደ ስራው እንዲገባ የሚያግዝ መሆኑንም አንስተዋል። የተተከለው ሻይ ለምርት እንዲደርስ ከመንከባከብ ጎን ለጎን የሻይ ምርት የማቀነባበሪያ ፋብሪካ የመገንባት ስራውም ቀጣይ አቅጣጫ መሆኑንም አክለዋል። ከዚሁ ጎን ለጎን የሻይ ልማቱን ለማስፋፋትም በክልሉ በሚቀጥሉት ጊዜያት የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት የተጀመረው የሻይ ልማት ስራ የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኢሉአባቦር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ ናቸው። በዚህ ወቅት ለደረሰው የሻይ ምርት የገበያ ትስስር ከመፍጠር ጎን ለጎን ቀጣይ የሚተከል ችግኝ ዝግጅት መጀመሩንም አስረድተዋል። በሀሉ ወረዳ ተደራጅተው በሻይ ልማት ስራ የተሰማሩት ወይዘሮ አበበች ደኑና አቶ ዮናስ አረጋ፣ የሻይ ምርታቸው ጥሩ ደረጃ ላይ መሆኑን ተናግረው ቀጣይ ስራውን ለማስፋፋት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
በጉራጌ ዞን እየተመዘገበ ያለውን የልማት ስኬት በማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትጋት እንሰራለን
Dec 9, 2025 37
ወልቂጤ፤ህዳር 30/2018 (ኢዜአ)፦በጉራጌ ዞን በመደመር መንግስት እይታ እየተመዘገበ ያለውን የልማት ስኬት በማስቀጠል የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትጋትና በቅንጅት እንደሚሰሩ የዞኑ አመራሮች ገለጹ። የመደመር መንግሥት እይታ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በማረጋገጥና ሁለንተናዊ ለውጥ በማምጣት ህዝብን የልማቱ ተጠቃሚ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም በገጠርና በከተማ ያሉ ፀጋዎችን ለይቶ በአዲስ እይታ በማልማት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ትኩረት ስለተሰጠው ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአመራሮች ስልጠና ማጠቃለያ ላይ የመደመር መንግስትን እሳቤ ባስረዱበት ወቅት ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ለማምጣት አዲስ እይታ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በተለይም በቴክኖሎጂ የተደገፈ የግብርና ልማት ማከናወን፣ ፆም የሚያድር መሬትን ወደ ምርት መቀየር እንዲሁም የግብርና እና ገጠር ሽግግር እምርታን ማምጣት እንደሚገባም በአፅንኦት ተናግረዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የጉራጌ ዞን አመራሮችም በዞኑ ያለውን ዕምቅ ፀጋ በመደመር መንግስት እይታ ወደውጤት በመቀየር ህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትጋትና በቅንጅት እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡ ለአመራር የተሰጠው ስልጠናም በየአካባቢው የተጀመሩ የልማት ውጥኖችን በትጋትና በላቀ ተነሳሽነት ለመፈጸም አቅም እንደፈጠረላቸው ነው የተናገሩት። በብልጽግና ፓርቲ የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አለማየሁ ገብረመስቀል እንደተናገሩት፤ ስልጠናው የልማት አቅምን ለይቶ ወደ ውጤት ለመቀየር የተጀመረውን ጥረት ለማሳደግ የሚያግዝ ነው። በተለይ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚን ለማረጋገጥ፣ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እንዲሁም የከተማ ነዋሪዎችን አኗኗር ለማሻሻል የሚያስችል እውቀትና ግንዛቤ በስልጠናው እንዳገኙ ገልጸው፣ በቀጣይም ለህዝብ ተጠቃሚነት ተግተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። የሀሳብና የተግባር አንድነትን ፈጥሮ ውጤታማ ልማት በማከናወን በኩል ከዚህ ቀደም ይታዩ የነበሩ ጉድለቶችን ለማረም በትኩረት እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬታማ የልማት ስራዎችን ለማሳደግም በቅንጅትና በትጋት ለመስራት መዘጋጀታቸውንም አረጋግጠዋል። በዞኑ በግብርና ዘርፍ ያለን እምቅ አቅም ወደውጤት ለመቀየርና የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ናቸው። ለዚህም ሳይታረሱ ጾም ያድሩ የነበሩ ማሳዎችና በባህር ዛፍ የለማን ማሳ አንስቶ በተለያዩ ሰብሎች፣ አትክልት፣ ፍራፍሬና የቅመማ ቅመም ምርቶች ለመሸፈን በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ የግብርና ልማት ሥራው ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ምርጥ ዘርና የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽነት ማጠናከር፣ እንዲሁም ለኩታ ገጠም የአስተራረስ ዘዴ ትኩረት እንደሚሰጥም አቶ አበራ ተናግረዋል። ስልጠናው የብልጽግና ጉዞን ለማፋጠን የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ግብአት ያገኙበት እንደሆነ የገለጹት የዞኑ የፋይናንስ መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ ሳሊም ከድር በበኩላቸው፣ የዞኑን ልማት በማፋጠን የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል።
በዞኑ ለቱሪዝም ልማት የሚውሉ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በመለየት የማልማት ሥራ ተጀምሯል
Dec 9, 2025 48
አዳማ ፤ህዳር 30/2018(ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ለቱሪዝም ልማት የሚውሉ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በመለየት የማልማት ሥራ መጀመሩን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። የመደመር መንግስት በየአካባቢው ያሉ እምቅ የቱሪዝም አቅሞችን በማልማት ወደ ውጤት እየቀየረ የቱሪዝም ዘርፉንም እያነቃቃ መምጣቱ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና በሰጡበት ወቅት "ቱሪዝምን ከቅርስነት ወደ ቁርስነት እንቀይረው፤ ቅርስ ስላለ ብቻ ቱሪስት መጥቶ አያይም፤ ለሚያወጣው ወጪ የሚመጥን አገልግሎት ይፈልጋል፤ የበለጠ ማልማት ያስፈልጋል" ብለው ነበር። ጠቅላይ ሚኒስተሩ በዚሁ መድረክ ላይ አንድ የቱሪስት መዳረሻ በዞን ደረጃ መኖር እንዳለበት አቅጣጫ ያስቀመጡ ሲሆን ሁሉም በየአካባቢው ያለውን እምቅ የቱሪዝም አቅም ለይቶ ማልማት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። በዚሁ ጉዳይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የምስራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አባቡ ዋቆ፣ በዞኑ ለቱሪዝም መዳረሻነት የሚውሉ መስህቦችን ለይቶ የማልማት ስራ ተጀምሯል ብለዋል። ዞኑ በሰቃ፣ ቆቃና ባቱን ጨምሮ የበርካታ ሐይቆች መገኛ መሆኑን ተናግረው በሐይቆቹ ዙሪያ እና አካባቢው የልማት ስራዎች መከናወን ጀምረዋል ነው ያሉት። በተለይ በቆቃ ሐይቅ ላይ የመሰረተ ልማት ዝርጋታና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ግንባታ እየተከናወነ ሲሆን በዚህም ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል መፈጠሩን አስረድተዋል። ሀይቁን ምቹ የቱሪዝም መዳረሻ ከማድረግ አንጻር ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ጠቅሰው በሌሎችም ሀይቆች ላይም ስራው ይቀጥላል ብለዋል። በሌላ በኩል ከገጠር ኮሪደር ልማት አንጻርም በዞኑ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራት የገጠሩን ህዝብ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። የኮሪደር ልማቱ አርሶ አደሩ የአኗኗር ዘይቤውን መቀየር እንዲችል የባዮጋዝ፣ የፀሐይ ሃይል፣ መብራት እና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎት ማግኘት እንዲችል ማድረጉን አስረድተዋል። ከሁሉም በላይ የአርሶ አደሩን የመኖሪያ አካባቢ ውብ እና ማራኪ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው ዘንድሮም ስራው በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል። በአጠቃላይ የግብርና ልማት ሥራ በተለይም በስንዴ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶና ሙዝን ጨምሮ በኢኒሼቲቭ መልክ የተገበሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አንስተዋል። በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብርም በእንስሳት እርባታ፣ በዶሮ እርባታና በከብት ማድለብ እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ልማቶች ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የግብርና ልማት ስራው ለኢንዱስትሪ ዘርፍ ግብዓት ሊሆን በሚችል መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አመልክተዋል። “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ የተሰጠው ስልጠናም የበለጠ የአካባቢያቸውን የልማት አቅሞች ወደ ውጤት ለመቀየር ያነሳሳቸው መሆኑን አስረድተዋል።    
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ መጠበቅ የሚያስችል የዲጂታል ሰርተፍኬት አገልግሎት ይፋ ሆነ
Dec 9, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ መጠበቅ የሚያስችል የዲጂታል ሰርተፍኬት አገልግሎትን በይፋ አስጀምሯል። አገልግሎቱ በይፋዊ ቁልፍ መሰረተ ልማት ውስጥ የፋይዳ ደህንነት ማስጠበቂያ ቁልፎች የሚፈጠሩበትና የሚንቀሳቀሱበትን አሰራር ያካተተ ነው ተብሏል።   እነዚህ ቁልፎች በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ ለመጠበቅ ጥቅም ላይ የሚውል የመተማመኛ ዲጂታል ፊርማ ለማዘጋጀት የሚውሉ መሆኑም ተገልጿል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ፤ ከዚህ ቀደም ለኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት የዲጂታል ሰርተፊኬት አገልግሎት መጀመሩን ገልጸው፤ ዛሬ በይፋ የተጀመረው የፋይዳ መታወቂያ ሰርተፊኬት አገልግሎት ቀጣይ ስራ ነው ብለዋል። የሰርተፊኬት አገልግሎቱ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በከፍተኛ የደህንነት ደረጃዎች ባላቸው ቴክኖሎጂዎች የተጠበቀ እንዲሆን ያግዛል ነው ያሉት። የማንነት ስርቆትን ለመከላከል፣ማጭበርበር እና የማንነት መረጃን አላግባብ መጠቀምን ለመከላከል የሚያስችል መሆኑንም አመልክተዋል። ደህንነቱ የተጠበቀ ዲጂታል መታወቂያ ጤና፣ ትምህርት፣ ባንክን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶች በተሻለ መልኩ ለማግኘት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው መሆኑም ነው የተገለጹት። የፋይዳን ደህንነት ማረጋገጥ ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ የተሳለጠ አገልግሎት እንዲኖር ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል።   የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያሥላሴ በበኩላቸው፤ 29 ሚሊዮን ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መመዝገባቸውን ተናግረዋል። መታወቂያ ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ደህንነቱን ማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ አኳያ የሰርተፊኬት አገልግሎቱ መጀመር ትልቅ እርምጃ ነው ብለዋል። የሰርተፊኬት አገልግሎቱ የፋይዳ ዲጂታል ሰነዶች ተዓማኒነትን የሚጨምር መሆኑንም ጠቁመዋል።
የመደመር መንግስት ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ጋራ ብልፅግና የተጀመረውን ጉዞ ለማሳካት በትጋት ይሰራል- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Dec 9, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግስት ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ጋራ ብልፅግና የተጀመረውን ጉዞ ለማሳካት፣ በመፍጠር፣ በመፍጠን እና በእመርታ መርሕ በትጋት እንደሚሰራ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዲጂታል ኢኮኖሚን መገንባት ምርጫ ሳይሆን ብልጫ ነው! በሚል ርዕስ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ሁለተኛውን የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤን በይፋ ማስጀመራቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በውጤታማነት መተግበሩ፣ ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎቶችን ተደራሽ ከማድረግ ባሻገር፣ የዕለት ከዕለት የኑሮ እንቅስቃሴን እያቀለለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተጨማሪም የኤሌክትሮኒክና የዲጂታል ግብይት ሥርዓትን ተመራጭ የክፍያ መንገድ እንዲሆን ማስቻሉን አመልክተዋል። ይሄም የሕዝብን ኑሮና የመንግሥትን አገልግሎት ከምርጫም በላይ ብልጫ ያለው እንዲሆን ያስችላል ነው ያሉት። ባለፉት አምስት ዓመታት በተዘረጋው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ውስጥ፣ በየዓመቱ ከ18.5 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ይሄንን ስኬት በላቀ መልኩ በማስቀጠል ሁሉን አቀፍ ብልፅግናን የማሳካት ግብ የያዘውን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በቅርቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁን አውስተዋል። ስትራቴጂው ዲጂታል መሠረተ ልማትን የማጠናከር፣ ተደራሽነትን ብቻ ሳይሆን አጠቃቀምን ለማስፋት ክሂሎትን የመገንባት እና ችግር ፈቺ ፈጠራን የማበረታታት ዓላማ ያለው መሆኑን ጠቅሰው ለስኬታማነቱ ሁሉም ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር መንግሥት ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ጋራ ብልፅግና የጀመርነውን ጉዞ ለማሳካት፣ በመፍጠር፣ በመፍጠን እና በእመርታ መርሕ ይተጋል ሲሉም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስና የክፍያ ሥርዓት በፈጣን የዕድገት ጎዳና ላይ ነው- የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)
Dec 9, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30፣ 2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስና የክፍያ ሥርዓት በፈጣን የዕድገት ጎዳና ላይ መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ። ከ2026 - 2030 የሚተገበረው ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ ዛሬ በሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህና ሌሎችም የመንግሥት ከፍተኛ አመራር አባላት በተገኙበት ይፋ ተደርጓል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ( ዶ/ር) በኢትዮጵያ የዲጂታል ለውጥ ከፍተኛ እድገት ላይ እንደሚገኝ በአፅንኦት ገልጸዋል። የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቶች ከፍተኛ ተቀባይነት እያገኙ እና ለኢኮኖሚ እድገት ጉልህ ሚና እያበረከቱ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ አስደናቂ የሆነ የዲጂታል ለውጥ እያስተናገደች መሆኗን ገልጸው፤ ይህም ለፋይናንስ ዘርፉ ዕድገት ትልቅ መስፈንጠሪያ እየሆነ መምጣቱን አንስተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ፈጠራን የሚያበረታቱ አሠራሮችና በዲጂታል መሠረተ ልማት ላይ እየተደረጉ ያሉ ኢንቨስትመንቶችም ለዕድገቱ ሚናቸው የላቀ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የዲጂታል ግብይቶች ፈጣን ዕድገት እያሳዩ ነው ያሉት የባንኩ ገዥ፤ ይህም በሀገሪቷ የግብይት ገጽታ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ማምጣቱን ጠቁመዋል። ይህ የዲጂታል ግብይት መጨመር፣ የዲጂታል ክፍያዎች ተቀባይነት እየጨመረ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑንም ተናግረዋል። በብሔራዊ የክፍያ መሠረተ ልማቶች ላይ እየተደረጉ ያሉ የማሻሻያ ሥራዎች ቅልጥፍናንና ደህንነትን እያሻሻሉ ሲሆን፤ ጠንካራ የዲጂታል ፋይናንስ ሥርዓት እንዲኖር መሠረት እየጣሉ ነው ብለዋል። ሰፊ የዲጂታል እምቅ አቅም ያላት ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ያለ የፋይናንስና የግብይት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን ገልጸዋል። እነዚህ ስኬቶች ቢኖሩም በቴክኖሎጂ ተደራሽነት ያሉ ክፍተቶች፣ የአጣዳፊ ጊዜ አገልግሎቶች አለመስፋት እና እያደጉ የመጡ የሳይበር ደህንነት ስጋቶችን ጨምሮ ፈተናዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። እነዚህን ፈተናዎች ለመፍታት በመንግሥት እና የግል ዘርፉ ትብብር አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የብሔራዊ ዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ (2026-2030) በፋይናንስ አገልግሎት ውስጥ አካታችነትን እንደሚያጎለብት እና ፈጠራን እንደሚያበረታታም ነው የገለጹት ገዥው። አዲሱ ስትራቴጂ አስተማማኝ እና ተዓማኒ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መዘርጋት፣ የፋይናንስ አገልግሎቶች ዲዛይን ውስጥ የፆታ አቀፍ ተጠቃሚነትን ማሳደግ እና ከድንበር ተሻጋሪ ክፍያዎች ጋር የሚጣጣም የክፍያ ስርዓትን መፍጠርን ያካትታል ብለዋል። በተጨማሪም ስትራቴጂው የብሔራዊ መረጃ ልውውጥ እንዲቋቋም እና የአስፈላጊ አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማስፋት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ጠንካራ ዲጂታል ኢኮኖሚ እየገነባች ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Dec 9, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ህዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ጠንካራ ዲጂታል ኢኮኖሚ እየገነባች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ፤ ከ2026 - 2030 የሚተገበረውን ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በተሳካ ሁኔታ በመተግበር ዘርፈ ብዙ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ተጨባጭ የዲጂታል እድገት ማስመዝገቧን ጠቅሰው፤ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት በሚያስደንቅ ፍጥነት መስፋፋቱን ተናግረዋል። መንግሥት በወሰዳቸው የሪፎርም እርምጃዎች እና የመሠረተ ልማት ግንባታ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ጠንካራ መሠረት መገንባቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ፋይናንስ ምህዳሩ በየዓመቱ ከ18 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይቶችን እያስተናገደ ነው ብለዋል። የዘርፉ ለውጥ ፈጣንና አስተማማኝ የቴሌኮምና የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማስፋት የኢኮኖሚውን ዲጂታል ጉዞ እያፋጠነ መሆኑን ገልጸዋል። የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያሉ የዲጂታል የመንግሥት አሠራሮች በመቶዎች የሚቆጠሩ አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ በማሳለጥ እንግልትን እየቀነሱና ግልጽነትን እያሻሻሉ መሆኑን ተናግረዋል። ብሔራዊ ባንክ አሠራሮችን በማዘመን ለሞባይል ገንዘብ ዝውውር፣ ለክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች እና ለፈጠራ ባለሙያዎች ምቹ ምህዳር መፍጠሩን ተናግረዋል። በኢት-ስዊች የተደገፈው ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ አሠራር ከፍተኛ ገንዘብ በባንኮች መካከል እና በዲጂታል አማራጭ በቀላሉ እንዲንቀሳቀስ አስችሏል ነው ያሉት። የቴሌብር ፈጣን ተደራሽነትና ለአጠቃቀም ምቹ መሆኑ የዕለት ተዕለት የዜጎችን ኑሮ እያሳለጠ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭን ጨምሮ ዲጂታል ክህሎትን የማጎልበት ሥራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው ተናግረዋል። በዲጂታል ዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢኮኖሚውን ወደ ፊት የሚያሻግሩ ብሔራዊ መሠረተ ልማቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ነገር ግን ከተደራሽነት ባሻገር ትርጉም ባለው አጠቃቀም ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል ነው ያሉት። የዲጂታል አጠቃቀምን ማሳደግ የአርሶና አርብቶ አደሮችን ህይወት በማሻሻል፣ ሥራቸውን በማቅለል፣ የፋይናንስ አገልግሎትን በቀላሉ እንዲያገኙ በማድረግ የአካታች ኢኮኖሚ ዕድገት ይፋጠናል ብለዋል። የዲጂታል ጉዟችን ቀጣዩ ምዕራፍ ሊለካ የሚገባው የህዝባችንን ህይወት በማሻሻል ረገድ ነው ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።   ከዚህ አኳያ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሠረተ ልማትን እንድናጠናክር፣ አጠቃቀምን ማስፋት፣ ክህሎቶችን መገንባት እና ችግሮችን የሚፈታ ፈጠራን የማበረታታት ዓላማ ያነገበ መሆኑን ገልጸዋል። ዘመኑን የዋጀው ይህ ስትራቴጂ፣ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና ማህበራዊ ዘርፎች ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ግብይት ማህበረሰቡን የሳይበር ደህንነትን በማረጋገጥ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት እና ኃላፊነት በተሞላበት አሠራር ህዝቡን ማገልገል እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በጋራ ዓላማ በማሳተፍ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚሆን ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የዲጂታል መፃኢ ዕድሏን የሚወስን ጠንካራ መሠረት አስቀድማ ገንብታለች ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በቀጣይ ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ተፅዕኖ እና ወደ ጋራ ብልጽግና የሚደረገውን ሽግግር ማፋጠን እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ስፖርት
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድሬዳዋ ከተማን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሁለተኛ ከፍ አደረገ 
Dec 9, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል። ረፋድ ላይ በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ረድኤት አስረሳኸኝ በ43ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥራለች። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ ቅድስት ዘለቀ የጨዋታ ኮከብ በመባል ተመርጣለች። በሊጉ ስምንተኛ ድሉን ያስመዘገበው የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች እየቀሩት በ25 ነጥብ ደረጃውን ከአራተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ12 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ ረድኤት አስረሳኸኝ በሊጉ ያስቆጠረቻቸውን ግቦች ወደ ዘጠኝ ከፍ በማድረግ ከኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰለሞን ቀጥላ በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ‘ የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከቦሌ ክፍለ ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋል።
የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከቦሌ ክፍለ ከተማ ጋር ይጫወታል 
Dec 9, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል። ከቀኑ 7 ሰዓት ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከቦሌ ክፍለ ከተማ በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ ያደረጋቸውን 10 ጨዋታዎች አሸንፏል። 28 ግቦችን በጨዋታዎቹ ላይ ሲያስቆጥር አምስት ግቦችን ተቆጥሮበታል። ቡድኑ በ30 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ተጋጣሚው ቦሌ ክፍለ ከተማ በሊጉ ባካሄዳቸው 10 ጨዋታዎች በአራቱ ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ አራት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይቷል። 11 ግቦችን ሲያስቆጥር 10 ጎሎችን አስተናግዷል። ቦሌ ክፍለ ከተማ በ16 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ያጠናክራል። ቦሌ ክፍለ ከተማ ካሸነፈ ተከታታይ ድሉን ያስመዘግባል። በሌላኛው መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከድሬዳዋ ከተማ በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ይጫወታሉ። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሊጉ ባከናወናቸው ስምንት ጨዋታዎች ሰባት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። በስምንቱ ጨዋታዎች ላይ 26 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ የተቆጠረበት ጎል አንድ ብቻ ነው። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች እየቀሩት በ22 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ ባካሄዳቸው 10 ጨዋታዎች አራቱን ሲያሸንፍ በስድስቱ ሽንፈትን አስተናግዷል። 10 ግቦችን ሲያስቆጥር 15 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ12 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካሸነፈ የሁለተኝነት ደረጃን ከሃዋሳ ከተማ ይረከባል። ተጋጣሚው ድሬዳዋ ከተማ በ10ኛ ሳምንት በቦሌ ክፍለ ከተማ ካጋጠመው ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል።
በሻምፒዮንስ ሊግ ባየር ሙኒክ ከስፖርቲንግ ሊዝበን ኢንተር ሚላን ከሊቨርፑል  የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ 
Dec 9, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የስድስተኛ ጨዋታ መርሃ ግብር ዛሬ ይጀመራል። ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ ባየር ሙኒክ ከስፖርቲንግ ሊዝበን በአሊያንዝ አሬና ስታዲየም ይጫወታሉ። ዘንድሮው በአውሮፓ መድረክ ጥሩ ግስጋሴ እያደረገ የሚገኘው ባየር ሙኒክ በ12 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ስፖርቲንግ ሊዝበን በ10 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። ባየር ሙኒክ ካሸነፈ ደረጃውን ወደ ሁለተኛ ከፍ ያደርጋል። ኢንተር ሚላን ሊቨርፑልን ምሽት አምስት ላይ በጁሴፔ ሚኤዛ ስታዲየም የሚያስተናግድበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። የጣልያኑ ቡድን በ12 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ሊቨርፑል በዘጠኝ ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የሶስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ኢንተር ሚላን እና የስድስት ጊዜ የዋንጫው ባለቤት ሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። በሌሎች መርሃ ግብሮች አትላንታ ከቼልሲ፣ ባርሴሎና ከኢንትራክት ፍራንክፈርት፣ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከስላቪያ ፕራግ፣ ፒኤስቪ አይንድሆቨን ከአትሌቲኮ ማድሪድ፣ ሞናኮ ከጋላታሳራይ እና ዩኒየን ሴይንት ጊሎይስ ከማርሴይ በተመሳሳይ ከምሽቱ አምስት ላይ ይጫወታሉ። ካይራት አልማቲ ከኦሎምፒያክስ ከምሽቱ 12 ሰዓት ከ30 ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ማንችስተር ዩናይትድ ዎልቭስን አሸነፈ
Dec 9, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 29/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 15ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሃ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ዎልቭስን 4 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በሞለኒው ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ብሪያን ምቡዌሞ እና ሜሰን ማውንት ቀሪዎቹን ጎሎችን ለዩናይትድ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ጂን-ራይሰነር ቤልጋርድ ለዎልቭስ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ላይ ማንችስተር ዩናይትድ በዎልቭስ ላይ ከፍተኛ ብልጫ ወስዶ የተጫወተ ሲሆን ተጨማሪ ግቦችን ማስቆጠር የሚችልበትን እድል አልተጠቀመበትም። በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ድሉን ያስመዘገበው ማንችስተር ዩናይትድ በ25 ነጥብ ደረጃውን ከ12ኛ ወደ 6ኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ 13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ዎልቭስ በሁለት ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። በከፍተኛ ውጤት ማጣት ቀውስ ውስጥ የሚገኘው ዎልቭስ በሊጉ ምንም ጨዋታ አላሸነፈም። በውጤቱ እጅጉን ደስተኛ ያልሆኑ አብዛኞቹ የዎልቭስ ደጋፊዎች ጨዋታው ከመጠናቀቁ በፊት ስታዲየሙን ለቀው ወጥተዋል። በ16ኛ ሳምንት ዎልቭስ ከሊጉ መሪ አርሰናል እና ማንችስተር ዩናይትድ ከቦርንማውዝ ይጫወታሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ረቂቅ አዋጁ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስራዎችን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ጉልህ ጠቀሜታ ይኖረዋል 
Dec 5, 2025 243
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 26/2018(ኢዜአ)፦የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ የሀገሪቱን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስራዎች የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ ገለጹ። በሕዝበ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት እና የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ይፋዊ ውይይት መድረክ አካሂደዋል።   በምክር ቤቱ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ በዚሁ ወቅት፤ የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ በተለያዩ አሰራሮች ላይ መኖሩን ጠቅሰዋል፡፡ አንድ ወጥ በሆነ አሰራር፣ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችና ሀገሪቱ ከደረሰችበት ደረጃ ጋር በተጣጣመ መልኩ ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱ አስፈላጊ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የሀገሪቱን የበለጸገ የስነ ምህዳር ሀብት ዘላቂ በሆነ ወጥ አሰራር ለማጠናከር የአገልግሎት ክፍያ ስርዓቱ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የደን ልማቶች የግብርና ምርታማነትን በማጎልበት አረንጓዴ ልማቶችን የበለጠ ውጤታማ ያደርጋል ብለዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የተፈጥሮ ሀብቶችን ጥበቃና እንክብካቤን በማጠናከር አካባቢ ላይ የሚደርሰውን ጉዳትና የህብረተሰቡን ተጋላጭነት መቀነስ አስፈላጊ ነው።   ረቂቅ አዋጁ ለመጀመሪያ ጊዜ መዘጋጀቱን ገልጸው፤ የተለያዩ ማህበረሰብ ክፍሎች አካባቢያቸውን በመጠበቃቸው ለአገልግሎታቸው ክፍያ እንዲያገኙ የሚያደርግ የማበረታቻ ስርዓት የሚዘረጋ ነው ብለዋል። ስነ ምህዳር ላይ ጉዳት የሚያደርሱ እንቅስቃሴዎችን ለመከላከል የአካባቢን ጥበቃ በዘላቂነት የሚያበረታታ ሂደትን የሚፈጥር አዋጅ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙ ባለ ድርሻ አካላት የስነ ምህዳር አገልግሎት አቅራቢዎች፣ ረቂቅ አዋጁ ላይ መካተት የሚገባቸውን ጉዳዮች፣ ግልጽነትን የሚጠይቁና ከትርጉም ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤በረቂቅ አዋጁ የስነ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ላይ የማህበረሰቡና የባለ ድርሻ አካላት ተጠቃሚነት፣ ተሳታፊነትና ፍትሃዊነት በግልጽ መቀመጡን ተናግረዋል። አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ የመንግስት ተቋማትና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት አገልግሎት አቅራቢዎች ይሆናሉ ብለዋል። ከግብርናና ከደን ልማት ጋር ተያይዞ የስነ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ አስገዳጅ የሆነባቸው አዋጆች መኖራቸውን ጠቅሰው ረቂቅ አዋጁ የክፍያ ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የፌደራልና የክልል ባለ ድርሻ አካላትን ሚና እና ሀላፊነትም በግልጽ አስቀምጧል ብለዋል።   በምክር ቤቱ የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር)፤ በረቂቅ አዋጁ ላይ አሻሚ ትርጉም የሚሰጡ፣ ግልጽነት የጎደላቸው ጉዳዮች ተሻሽለው ጠንካራ አዋጅ እንዲወጣ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።
በኢሉባቦር ዞን በክረምቱ ወቅት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ እየተከናወነ ነው
Dec 2, 2025 326
መቱ ፤ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፡-በኢሉባቦር ዞን በክረምቱ አረንጓዴ አሻራ መርሐግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በዘመቻ መልክ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የዞኑ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ሰራተኞች የተሳተፉበት በክረምቱ ወቅት የተተከሉ ችግኞችን በጋራ እየተንከባከቡ ናቸው። የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አወል መሐመድ በዞኑ በክረምቱ ወራት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰዋል። የችግኞቹን የጽድቀት መጠን ለማሳደግም ህብረተሰቡ እንክብካቤ እንዲያደርግ ግንዛቤ በመፈጠሩ የዞኑ የመንግስት ሰራኞችን ጨምሮ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍሎች ባሳተፈ መልኩ እንክብካቤው በዘመቻ መልክ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም የጽድቀት መጠናቸው በአሁኑ ወቅት ከ95 በመቶ በላይ መድረሱን ተናግረዋል። ለችግኞቹ የሚደረገው እንክብካቤ ጽድቀታቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ በአጭር ግዜ ደርሰው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው እንዲጎላ እንደሚያግዝም አመልክተዋል። በችግኝ እንክብካቤው ከተሳተፉ የመንግስት ሰራተኞች መካከል የዞኑ የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽሕፈት ቤት ባለሞያ አቶ መላኩ ከበደ በበኩላቸው በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአንድነት የተከልናቸውን ችግኞች በአንድነት የመንከባከብ ስራ እየሰራን ነው ብለዋል። በመንግስት አገልግሎት ለህዝብ ከሚሰጧቸው አገልግሎት ባለፈ በክረምቱ ወራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከሏቸውን ችግኞች በመንከባከብ እንዲጸድቁ ለማድረግ በስፍራው መገኘታቸውን ገልጸዋል። በአረንጓዴ አሻራ የተከልሏቸው ችግኞች የሚጠበቀውን ውጤት ለማግኘት መትከል ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የእንክብካቤ ስራውን ማጠናከር በማስፈለጉ ለዚሁ ተግባር መጥቻለሁ ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ፋጡማ የሱፍ ናቸው። አቶ እንዳሻው ጆቴ በበኩላቸው የተተከሉ ችግኞችን በጋራ በመንከባከብ ለውጤት ለማብቃት ያልተቋረጠ ክትትል በማስፈለጉ በተከላ ወቅቱ የገቡትን ቃል በተግባር ለማዋል ስራው ላይ መገኘታቸውን ጠቁመዋል። በክረምቱ የተተከሉት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተገቢው እንክብካቤ ካልተደረገላቸው በመጥፋት የወጣባቸው ከፍተኛ ገንዘብ ለብክነት እንደሚዳረግም አክለዋል።  
ኢትዮጵያውያን የደመቁበት የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ
Dec 1, 2025 335
ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ ተከናውኗል። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ የሽልማት መርሃ ግብሩ የሚዲያ አጋር ሲሆን የሁለት ቀኑን የሽልማት መርሃ ግብር የቀጥታ ስርጭት ሽፋን በመስጠት ለመላው አፍሪካውያን ተደራሽ አድርጓል። የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ(አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ አድርጓል። የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያን ጎብኝተዋል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች ተከናውኗል። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ያስገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ከ94ቱ ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ሶስቱ በተለያዩ ዘርፎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ አሸናፊ በመሆን ሽልማቱን ተቀብሏል። ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ ሽልማቱን የተጎናጸፈው “Climate Intelligence for Survival: IGAD’s Push for Accurate, Actionable Data” በሚል ርዕስ በጻፈው ጽሁፍ ነው። የጋዜጠኛ ጌትነት ጽሁፍ በኢጋድ ቀጣና ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና የሚዳስስ ነው። በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰት ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋዎችና ኢ-ተገማች የአየር ጸባይ ለውጦች ዜጎችን በማፈናቀል እና በቁም እንስሳት ላይ ያደረሱትን ጉዳት ይቃኛል። ትክክለኛ፣ ጊዜውን የጠበቀና ለተግባር ምላሽ የሚያገለግሉ የአየር ንብረት መረጃዎች የማይበገር አቅም ለመገንባትና አደጋዎችን ለመከላከል ያላቸውን ሚናም ተዳሷል። በጽሁፉ ላይ የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያና ትግበራ ማዕከል(ICPAC) የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን በማጠናከር፣ የትንበያ አቅም ማሳደግና የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት የመቋቋም አቅም ላይ እያከናወነ ያለው ስራ ተቀምጧል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች፣ የአንበጣ መንጋ፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብና ሌሎች ፈተናዎችን ለመከላከል ተአማኒነት ያለው የአየር ንብረት መረጃ ወሳኝ መሆኑም ተመላክቷል። በተለይም ኑሯቸው በተለያዩ ወቅቶች ላይ ለተመረኮዙ አርሶ እና አርብቶ አደሮች መረጃው ወሳኝ መሆኑን ያስቀምጣል። ሌላኛው ተሸላሚ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤ) ጋዜጠኛ ሽመክት ጉግሳ ነው። የተሸለመበት ዘርፍ በኦሮምኛ ቋንቋ በሰራው ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሙ ዛፎች ከሰው ህይወት ጋር ያላቸውን ቁርኝት በዋናነት ይቃኛል። መንደርደሪያውን ከዓለም የዛፍ ጠቀሜታና ጥበቃ በማድረግ በኦሮሚያ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ይዳስሳል። ዛፍ መትከል ተፈጥሮና የሰው ልጅን እንዴት እንደሚጠብቅ በተቃራኒው መቁረጥ የሚያደርሰውን ጉዳትም ያስቃኛል። የ21 ደቂቃ ፕሮግራሙ የኦሮሞ ህዝብ በዘመናት መካከል ዛፎችና የደን ሀብቶች እንዲጠበቁ ያደረገው አስተዋጽኦ ተወስቶበታል። በተለይም በገዳ ስርዓት ውስጥ ዛፍን መጠበቅ ያለው ሚና በስፋት ተነስቷል። አንድ ዛፍ ለአራት ሰዎች መኖር መሠረት ይሆናል፤ ዛፍ መቁረጥ አራት ሰዎችን እንዲሞቱ ያደርጋል የሚል የአባገዳ አስተያየትም ተጠቃሽ ነው። አባ ገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ እናቶችና የአካባቢ ማህበረሰቦች ተፈጥሮን ጠብቆ በማቆየት ያላቸው ሚና ቁልፍ እንደሆነ ተመላክቷል። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መስራችና ስራ አስኪያጅ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተበርክቶላታል። ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በሬዲዮ ጋዜጠኝነት ግንባር ቀደምና በዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቷንም ኢጋድ ገልጿል። በብሮድካስት ሚዲያው ከ40 ዓመት በላይ የቆየችው ጋዜጠኛ መዓዛ ሸገር ኤፍኤም 102.1ን ከ18 ዓመታት በፊት በማቋቋም በኢትዮጵያ ቀዳሚ የመረጃ እና የመዝናኛ ጣቢያ እንዲሆን ማድረጓ አመልክቷል። ከጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ አበይት ፕሮግራሞች መካከል “ማንን ምን እንጠይቅልዎ?” እና “ሸገር ካፌ” ተጠቃሽ ናቸው። ጋዜጠኛዋ በፕሮግራሞቹ ህዝብን ከመንግስት አገልግሎቶች ጋር በማገናኘትና በማህበራዊ፣ የህግ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ላይ የተመረኮዙ ውይይቶች እንዲካሄዱ መድረክ መፍጠር መቻሏንም ነው የገለጸው። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መሪ ሀሳብ በሆነው የእናንተ ሬዲዮ መዓዛ በጋዜጠኝነት ሙያ ህዝብን ለማገልገልና የኢትዮጵያውያንን ድምጽ ለማጉላት ያላትን ቁርጠኝነት ኢጋድ አድንቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ኢጋድ አመልክቷል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 1, 2025 319
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንደገለፀው በሚቀጥሉት አሥር ቀናት ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት አካባቢዎች ላይ ቀጣይነት ይኖረዋል። ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጥቂት የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናቶች ላይ በተዳከመ ሁኔታ ቀጣይነት ይኖራቸዋል። በዚህም የደቡብ ኦሮሚያ ዞኖች፤ የሲዳማ ክልል ዞኖች፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡባዊ ዞኖች እና የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ዞኖች በጥቂት ስፍራዎቻቸው ላይ በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙ ገልጿል። በሌላ በኩል ከሚኖረው የደመና ሽፋን ላይ በመነሳት በጥቂት የሰሜን፣ መካከለኛውና ደቡብ ጎንደር ዞኖች፣ ባህርዳር ዙሪያ፣ አዊ ፣ በምዕራብና ምስራቅ ጎጃም አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናት ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ትንበያው አብራርቷል። የምዕራብ ኦሮሚያ ክልል ዞኖች፣ አርሲ እና ምዕራብ አርሲ፤ ባሌ እና ምስራቅ ባሌ ዞኖች፣ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ እና የማኦኮሞ ልዩ ዞን፤ የጋምቤላ ክልል ዞኖች፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዞኖችም አልፎ አልፎ ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ። ስለሆነም በሚኖሩት ደረቅ ቀናቶች የደረሱ ሰብሎች መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል። በሌላ በኩል ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩም በመግለጫው ተብራርቷል። በዚህም የበጋው ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በተለይም በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መካከለኛውና ደቡብ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የለሊትና የማለዳው ቅዝቃዜ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን ትንበያው ያሳያል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 339
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል።   በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው።   አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 354
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 708
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 596
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ሐተታዎች
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 545
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 754
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 782
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 829
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 172
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2832
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2776
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3671
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2092
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1362
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7179
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5670
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57881
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52650
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33336
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30859
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26725
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25463
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25040
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25025
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57881
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52650
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33336
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30859
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 518
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው።   እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም።   የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል።   የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል።   ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!
ብልህ ከችግር ይማራል!!
Dec 2, 2025 344
ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል!! በማሙሽ ጋረደው ገራድ ተስፋዬ ተፈራ ትውልድና እድገታቸው በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ቃልሻ ቀበሌ ሲሆን በ1999 ዓ.ም በህገ ወጥ መንገድ ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው እንደነበር ያስታውሳሉ። ገንዘብ ለማግኘትና የመለውጥ ህልማቸውን ለማሳካት በሚል ሩቅ አስበው የጀመሩት ህገ ወጥ ጉዞ መዳረሻውን እስር ቤት አደረገው። ይህም ሁኔታ ''ሩቅ አሳቢ-ቅርብ አዳሪ'' አደረጋቸው። በባዕድ አገር በነበራቸው የ2 ዓመት የእስር ቤት ቆይታም የምግብ እጦትን ጨምሮ አካላዊ ጥቃትና ጉልበት ብዝበዛ እንዲሁም የተለያዩ ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶችን እንዳስተናገዱ ይናገራሉ።   ይህም አልበቃ ብሎ ከአካባቢው በህገወጥ መንገድ የሚሰደዱ ወጣቶችን ጉልበት በመጠቀም ሰፋፊ እርሻዎች ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ የጉልበት ብዝበዛ ይፈፀምባቸው እንደነበርም ያስታውሳሉ። ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል! የሚሉት ገራድ ተስፋዬ ሩቅ ሳይጓዙ፣ ገንዘብ ሳያወጡ ሰርተው መለወጥ የሚችሉበትን አካባቢያቸውን ፀጋ ሳያማትሩ ስደት መሄዳቸው ቁጭት ፈጥሮባቸው ነበር፡፡ ይህም በሀገራቸው እንኳንስ የለማን መሬት ይቅርና የተቦረቦረ መሬትን አልምቶ ጉልበትንና ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል ከእስር ቤት ቆይታቸው ተምረው ከእስር እንደተፈቱም ወዲያውኑ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል። በ2001 ዓ.ም ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሱም በማህበር ተደራጅተው ከመንግሥት ባገኙት 70 ሺህ ብር ብድር በእንስሳት እርባታ ላይ ለመሰማራት 4 የወተት ከብቶችን ገዝተው የእርባታ ስራ መጀመራቸውን ይገልጻሉ፡፡   በዚህም የዞኑ አስተዳደር የሰጣቸውን መሬት አልምተው የእንስሳት እርባታውን አስፋፍተው መስራት ጀመሩ፡፡ አሁን ላይ የወተት ላሞቹን ቁጥር 37 በማድረስ የወተት ምርታማነታቸው አድጎ ከቤት ፍጆታ አልፎ ለሆሳዕና ከተማና አካባቢው በቀን ከ670 ሊትር በላይ ወተት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ለ40 ወጣቶችም ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ከመፍጠራቸውም ባሻገር የተለያዩ የጭነትና የስራ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራት መቻላቸውን ይናገራሉ። የጀመሩትን ስራ በጥምር ግብርና የማስፋትና የሚያገኙትን ወተት በማቀነባበር ምርቱን በተለያየ መልኩ ለገበያ የማቅረብ ራዕይን ሰንቀው በትጋት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በህገወጥ ስደት ካጋጠማቸው ችግር ተነስተው በተግባር ያዩትን ለሌሎች በማስተማር የስደትን አስከፊነት ለአካባቢያቸው ወጣቶች እያስገነዘቡ መሆኑን ገልጸዋል።   ወጣቶች የስደትን አማራጭ ከመመልከታቸው በፊት የአካባቢያቸውን ፀጋ እንዲቃኙና ራዕይ ሰንቀው ራሳቸውን ለማሻሻል እንዲሰሩም መክረዋል። መለወጥ በውጪ ሀገር ብቻ ያለ የሚመስላቸው የቤተሰብ ኃላፊዎችም ልጆቻቸው በሀገራቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ በማመን ሊያግዟቸው እንደሚገባም አቶ ገራድ አስገንዝበዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደስላሴ፤ በክልሉ በርካታ ወጣቶች ያልተጨበጠ ተስፋ ሰንቀው ለህገወጥ ስደትና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡   በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ የሚያስችል አቅም በግብርናው ዘርፍ መኖሩን ጠቅሰው በዘርፉ የተሰማሩ ከስደት ተመላሾች በአካባቢያቸው ሰርተው ለስኬት እየበቁ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ላይ የሚገኙና የእነዚህን አካላት ተሞክሮ በመውሰድ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም