ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ አዲስ ድንቅ ስጦታ አበርክታለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 28, 2026 300
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ አዲስ ድንቅ ስጦታ አበርክታለች ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ አዲስ አበባችን የነዋሪዎቿን ጥያቄዎችና መሠረታዊ ፍላጎቶች በተጨባጭ እየመለሰች፣ ለሕዝባችን ቅድሚያ የሚሰጣቸውንና ከተማዋ የሚመጥናትን ታላላቅ የልማት ሥራዎች ሁሉ በላቀ ብቃትና ትጋት እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል። ዛሬ ለከተማችን አዲስ አበባ ድምቀትና ተጨማሪ ጌጥ እና የውበት ፀዳል ያላበሰውን ይህን የወንዝ ዳርቻ እና የግድብ ልማት በጠቅላይ ሚኒስትራችን ሐሳብ አመንጪነት በተሰጠን የሥራ መመሪያ መሠረት በጥራትና በፍጥነት አጠናቀን ለሕዝብ አቅርበናል ሲሉም ገልጸዋል።   ፕሮጀክቱ በከተማዋ ከተሰሩት ሌሎች የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች ጋር ተዋህዶ ሲታይ በእርግጥም አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርጧ የቱሪስት መዳረሻ ብቻ ሳትሆን የውበት ማማ የሚያደርጋት ድንቅ ፕሮጀክት መሆኑን ከንቲባዋ ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 87.6 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሲሆን፣ 10.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው፤ በውስጡም እጅግ ማራኪ የሆኑ የጋራ አገልግሎት መስጫዎችንና የሕዝብ መገልገያዎችን አሟልቶ ይገኛል ብለዋል፡፡ ይህም 1 ትልቅ ግድብ፣ 16 አነስተኛ ግድቦች፣ 3 ቼክ ዳሞች፣ 1.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሐይኪንግ፣ እንዲሁም 20.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ ድጋፍ ግድግዳን (Retaining Wall) ማካተቱን አንስተዋል።   የተፈጥሮ ውበቱን ይበልጥ ለማጉላትም 3 ማራኪ ፏፏቴዎች እና 1 የውሃ ምንጭ ግንባታ የተከናወነ ሲሆን፣ የመሬት ጥበቃን ለማረጋገጥ 36,928 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው የኮንሶ ጋቢዮንና የኮንሶ እርከን ሥራዎች ተሠርተውለታል ብለዋል፡፡ ልማቱ ለተፈጥሮ በሰጠው ልዩ ትኩረት፣ 59.7 ሄክታር የሚሸፍን ውብ የአረንጓዴ ልማት ስፍራን ያበለፀገ ሲሆን፣ 50,330 የተለያየ ዝርያ ያላቸው ዛፎችም እንደተተከሉበት ገልጸዋል። ከመሠረተ-ልማት አቅርቦት አኳያ 10.62 ኪሎ ሜትር ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ፣ 33.2 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገዶች፣ እና 33.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ዘመናዊ የመንገድ መብራት ዝርጋታ መከናወኑን አንስተዋል።   በተጨማሪም 19.13 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ እና የጎርፍ ማስወገጃ መስመር፣ እንዲሁም 23 ንፁህ የመጸዳጃ ቤቶች ተገንብተዋል። ጎብኚዎች ወንዙን በቀላሉና በውበት እንዲሻገሩ ለማስቻል 21 የእግረኛ ድልድዮች፣ 3 ተንጠልጣይ ድልድዮች፣ 6 የእግረኛ የብረት ድልድዮች፣ 1 ሰርኩላር ድልድይ እና 1 የኮንክሪት ድልድይ ተሠርተዋል። ማኅበረሰቡ ዘና እንዲልና የተሟላ አገልግሎት እንዲያገኝ በማሰብም፤ 9 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ በአንድ ጊዜ 695 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ 7 የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች (ፓርኪንጎች)፣ 4 የመሰብሰቢያ ስፍራዎች፣ 7 ፕላዛዎች እና 4 ፓቪሊዮኖች ተገንብተዋል። ለንግድና ለመዝናኛ አገልግሎት የሚውሉ 32 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ሱቆች፣ 2 አንፊ ቲያትሮች (Amphitheaters)፣ 10 ካፌቴሪያዎች፣ 7 የልጆች መጫወቻ ስፍራዎች፣ እንዲሁም 2 አነስተኛ የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት ተካተውበታል።   ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በታለመለት የጊዜ እና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ ሌሊት ከቀን የደከማችሁና የታተራችሁ፣ ያስተባበራችሁና የደገፋችሁ በየደረጃው የምትገኙ አመራሮች፣ እንዲሁም ለመላው የአካባቢው ማኅበረሰብ በከተማ አስተዳደሩ እና በራሴ ስም ላቅ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)  የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን መረቁ
Jun 28, 2026 210
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ይህ ሰፊ መሰረተ ልማት የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎችን በጋራ የያዘ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለት የተመረቀው ፕሮጀክት 87 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት የሚሸፍን መሆኑን የገለጹ ሲሆን 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት እንዳለው አመልክተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ የግንባታ ስኬት ብቻ ሳይሆን መዲናዋን የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋምና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች፣ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ የጀመርነውን ስልታዊ ሽግግር የሚያፋጥን ታላቅ አጋጣሚ ነው ብለዋል። ‎ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡
መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አካዳሚያዊ ነፃነት የሚያጎናጽፍ የራስ ገዝ አስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋት ምቹ ዕድል ፈጥሯል 
Jun 28, 2026 291
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አካዳሚያዊ ነፃነት የሚያጎናጽፍ የራስ ገዝ አስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋት ምቹ ዕድል መፍጠሩን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስክና ደረጃዎች ያሰለጠናቸውን 2 ሺ 882 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡   በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ (ዶ/ር)፣ የዩንቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተሾመ ነቃጥበብ(ዶ/ር)፣ የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ አባላትና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ (ዶ/ር) በሥነ-ሥርዓቱ እንደገለጹት፤ መንግስት እየሰራቸው ካሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል በትምህርት ዘርፉ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል። በዚህም መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አካዳሚያዊ ነፃነት የሚያጎናጽፍ የራስ ገዝ አስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋት ምቹ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ምሩቃኑ በተመረቁበት የትምህርት መስክ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በታማኝነትና ቅንነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋልም ብለዋል። በቀጣይም ተመራቂዎች ራሳቸውን በእውቀት በማብቃት በሀገራቸው የልማት ስራ ንቁ ተሳታፊ በመሆን የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ተሾመ ነቃጥበብ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዛሬ ተመራቂዎች እዚህ መድረስ የብዙ ድካም እና ጥረት ውጤት መሆኑን ገልፀው የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።   ዩኒቨርሲቲው ስር ሰዶ የቆየውን የትምህርት ጥራት እድገት ጉድለትን ለመፍታት ሙሉ ትኩረቱ ሰጥቶ በሰራቸው ስራዎች ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ዩኒቨርሲቲው ከሀገር ውስጥና ከጎረቤት ሀገራት ጭምር ተማሪዎችን በመቀበል ጥራት ያለው ትምህርት በመስጠት በርካታ ምሁራንን እያፈራ መሆኑን ገልጸዋል። በዩንቨርሲቲው የፊዚክስ ትምህርት ክፍል ከፍተኛ የማዕረግ ተመራቂ ኤርሚያስ አወቀ፤ በትጋት በማጥናት ለቀጣይ ህይወቱ ስንቅ የሚሆን ከፍተኛ የትምህርት ውጤት አምጥቶ ለምርቃት መብቃቱ እንዳስደሰተው ገልጿል።   ሌላኛዋ ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል 3 ነጥብ 81 በማስመዝገብ ከፍተኛ ውጤት ምሩቅ ሰላማዊት አበራ፤ የቤተሰብ ኃላፊነትን ከትምህርት ጋር በማጣመር ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባ በመመረቋ ኩራት እንደሚሰማት ተናግራለች።   የአካውንቲንግና ፋይናንስ ትምህርት ክፍል 3 ነጥብ 99 በማምጣት የማዕረግና የሜዳሊያ ተሸላሚው ሀለፎም አብርሀ በበኩሉ፤ የመምህራን እገዛና ጊዜውን በአግባቡ መጠቀሙ በከፍተኛ ውጤት ለመመረቅ መብቃቱን አንስቷል።   በቀጣይም በትምህርት ቆይታቸው የሸመቱትን ዕውቀትና ክህሎት ህዝባቸውንና ሀገራቸውን በታማኝነት ለማገልገል እንደሚጠቀሙበት ምሩቃኑ አረጋግጠዋል።
ሸገር ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ መቆየቱን አረጋገጠ
Jun 28, 2026 275
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሸገር ከተማ መቻልን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍቅሩ አለማየሁ እና ያሬድ መኮንን ግቦቹን አስቆጥረዋል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን ያስመዘገበው ሸገር ከተማ በ47 ነጥብ ከነበረበት 15ኛ ደረጃ ወደ 10ኛ ከፍ ብሏል። ዘንድሮ ከከፍተኛ ሊግ ያደገው ሸገር ከተማ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል። በሊጉ ዘጠነኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቻል በ56 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሃዋሳ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሀሰን ሁሴን በ34ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪ ሆኗል። ጌታነህ ከበደ በ61ኛው ደቂቃ የሃዋሳ ከተማን የአቻነት ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ51 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ሃዋሳ ከተማ በ50 ነጥብ ስምንት ደረጃ ላይ ይገኛል። ዛሬ አስቀድመው በተደረጉ የ37ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና ባህር ዳር ከተማን 1 ለ 0፣ ወላይታ ድቻ አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፈዋል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 37ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የፕሪሚየር ሊጉ የመጨረሻ ሳምንት (38ኛ ሳምንት) መርሐ ግብር በቀጣይ ሳምንት ይካሄዳል።
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን ማጎልበት አለባቸው
Jun 28, 2026 443
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን ማጎልበት እንደሚገባቸው የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ ገለፁ። ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፣ከሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ እና ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር ለሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል። የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ፣ መልካም እሴቶች እንዲጎለብቱ እና ህዝቡ በክልሉ በሚከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የሚያደርገውን ተሳትፎ ማሳደግ ያስቻሉ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል። በተለይም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ፅንፈኛ ሀይሎች በማህበረሰቡ መካከል የሚነዙትን የጥላቻና ሀሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል አሰባሳቢና ገዢ ትርክቶች እንዲሰርጹ በማድረግ ረገድ አበረታች ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም አፍራሽ የሆኑ ፕሮፖጋንዳዎችን ቀድሞ በመከላከል የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅና ሕብረ ብሄራዊነት እንዲሰርፅና እንዲፀና በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች በክልሉ በሁሉም ዘርፎች ለተመዘገቡ ውጤቶች አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም አንስተዋል። በተጨማሪም የህዝብ ሰላምና አንድነት እንዲጎለብትና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አዎንታዊ ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል። የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናም በባለሙያዎቹ ዘንድ የሚታዩ ውስንነቶችን ለመቅረፍና ግንዛቤ ለማጎልበት ከፍተኛ እገዛ አለው ብለዋል። ተቋሙ ለህብረተሰቡ ወቅታዊ መረጃዎችን ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ለሚመለከታቸው አካላት መሰል ስልጠናዎች የመስጠት ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አቶ አለምሸት ተሾመ በበኩላቸው፥ ከዩኒቨርሲቲው የሚገኝ ዕውቀት የአካባቢውን ማህበረሰብና ተቋማት እንዲጠቅም በተለያዩ መንገዶች እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በሀረሪ ክልል ለሚገኙ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች የተሰጠው ስልጠናም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል። መደበኛ የሚባለው የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ መረጃዎቹ ተደራሽ የሚደረግላቸው ማህበረሰቦችን ነባራዊ ሁኔት በመለየት መልዕክቶችን ማስተላለፍ እንደሚገባ አቶ አለምሸት ገልፀዋል፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች መልዕክት በመቅረፅና የማስተላለፊያ ቴክኖሎጂዎች አጠቃቀም ላይ ራሳቸውን ሊያበቁ ይገባል ብለዋል። ሐረማያ ዩኒቨርሲቲም የባለሙያዎቹን አቅም ለመገንባት የበኩሉን አስተዋፅዖ እንደሚያበረክት ተናግረዋል። ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።
የሚታይ
አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ አዲስ ድንቅ ስጦታ አበርክታለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 28, 2026 300
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ አዲስ ድንቅ ስጦታ አበርክታለች ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ አዲስ አበባችን የነዋሪዎቿን ጥያቄዎችና መሠረታዊ ፍላጎቶች በተጨባጭ እየመለሰች፣ ለሕዝባችን ቅድሚያ የሚሰጣቸውንና ከተማዋ የሚመጥናትን ታላላቅ የልማት ሥራዎች ሁሉ በላቀ ብቃትና ትጋት እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል። ዛሬ ለከተማችን አዲስ አበባ ድምቀትና ተጨማሪ ጌጥ እና የውበት ፀዳል ያላበሰውን ይህን የወንዝ ዳርቻ እና የግድብ ልማት በጠቅላይ ሚኒስትራችን ሐሳብ አመንጪነት በተሰጠን የሥራ መመሪያ መሠረት በጥራትና በፍጥነት አጠናቀን ለሕዝብ አቅርበናል ሲሉም ገልጸዋል።   ፕሮጀክቱ በከተማዋ ከተሰሩት ሌሎች የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች ጋር ተዋህዶ ሲታይ በእርግጥም አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርጧ የቱሪስት መዳረሻ ብቻ ሳትሆን የውበት ማማ የሚያደርጋት ድንቅ ፕሮጀክት መሆኑን ከንቲባዋ ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 87.6 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሲሆን፣ 10.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው፤ በውስጡም እጅግ ማራኪ የሆኑ የጋራ አገልግሎት መስጫዎችንና የሕዝብ መገልገያዎችን አሟልቶ ይገኛል ብለዋል፡፡ ይህም 1 ትልቅ ግድብ፣ 16 አነስተኛ ግድቦች፣ 3 ቼክ ዳሞች፣ 1.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሐይኪንግ፣ እንዲሁም 20.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ ድጋፍ ግድግዳን (Retaining Wall) ማካተቱን አንስተዋል።   የተፈጥሮ ውበቱን ይበልጥ ለማጉላትም 3 ማራኪ ፏፏቴዎች እና 1 የውሃ ምንጭ ግንባታ የተከናወነ ሲሆን፣ የመሬት ጥበቃን ለማረጋገጥ 36,928 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው የኮንሶ ጋቢዮንና የኮንሶ እርከን ሥራዎች ተሠርተውለታል ብለዋል፡፡ ልማቱ ለተፈጥሮ በሰጠው ልዩ ትኩረት፣ 59.7 ሄክታር የሚሸፍን ውብ የአረንጓዴ ልማት ስፍራን ያበለፀገ ሲሆን፣ 50,330 የተለያየ ዝርያ ያላቸው ዛፎችም እንደተተከሉበት ገልጸዋል። ከመሠረተ-ልማት አቅርቦት አኳያ 10.62 ኪሎ ሜትር ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ፣ 33.2 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገዶች፣ እና 33.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ዘመናዊ የመንገድ መብራት ዝርጋታ መከናወኑን አንስተዋል።   በተጨማሪም 19.13 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ እና የጎርፍ ማስወገጃ መስመር፣ እንዲሁም 23 ንፁህ የመጸዳጃ ቤቶች ተገንብተዋል። ጎብኚዎች ወንዙን በቀላሉና በውበት እንዲሻገሩ ለማስቻል 21 የእግረኛ ድልድዮች፣ 3 ተንጠልጣይ ድልድዮች፣ 6 የእግረኛ የብረት ድልድዮች፣ 1 ሰርኩላር ድልድይ እና 1 የኮንክሪት ድልድይ ተሠርተዋል። ማኅበረሰቡ ዘና እንዲልና የተሟላ አገልግሎት እንዲያገኝ በማሰብም፤ 9 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ በአንድ ጊዜ 695 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ 7 የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች (ፓርኪንጎች)፣ 4 የመሰብሰቢያ ስፍራዎች፣ 7 ፕላዛዎች እና 4 ፓቪሊዮኖች ተገንብተዋል። ለንግድና ለመዝናኛ አገልግሎት የሚውሉ 32 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ሱቆች፣ 2 አንፊ ቲያትሮች (Amphitheaters)፣ 10 ካፌቴሪያዎች፣ 7 የልጆች መጫወቻ ስፍራዎች፣ እንዲሁም 2 አነስተኛ የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት ተካተውበታል።   ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በታለመለት የጊዜ እና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ ሌሊት ከቀን የደከማችሁና የታተራችሁ፣ ያስተባበራችሁና የደገፋችሁ በየደረጃው የምትገኙ አመራሮች፣ እንዲሁም ለመላው የአካባቢው ማኅበረሰብ በከተማ አስተዳደሩ እና በራሴ ስም ላቅ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)  የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን መረቁ
Jun 28, 2026 210
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ይህ ሰፊ መሰረተ ልማት የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎችን በጋራ የያዘ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለት የተመረቀው ፕሮጀክት 87 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት የሚሸፍን መሆኑን የገለጹ ሲሆን 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት እንዳለው አመልክተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ የግንባታ ስኬት ብቻ ሳይሆን መዲናዋን የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋምና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች፣ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ የጀመርነውን ስልታዊ ሽግግር የሚያፋጥን ታላቅ አጋጣሚ ነው ብለዋል። ‎ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 565
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ህልሞቻችን እስከሚሳኩ በብርታት እንሠራለን - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 28, 2026 537
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ)፡- በሁሉም መስክ አቅደን የምንተገብራቸው ህልሞቻችን እስከሚሳኩ ድረስ በብርታት እንሠራለን ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ አረንጓዴ ዐሻራ ከእሳቤ እስከ ትግበራው ኢትዮጵያ የተገለጠችበት ደማቅ ብሔራዊ ቀለም ነው ብለዋል። በእሳቤዎች የተመሩ የታላላቅ ስልጣኔዎች እና የነጠሩ እውቀቶች ማሕደር በሆነችው ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ እሳቤ ይህ ትውልድ የአርቆ አሳቢ አባቶቹ ልጅ መሆኑን ያስመሰከረበት የጠራ ሐቅ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። የአየር ንብረት ለውጥ በተለምዶ ከምናየው ተደጋጋሚ የኮንፈረንስ እቅድ በተሻገረ፤ አፈር ነክቶ ጭቃ ረግጦ በትጋት በመስራት የሚመጣ የትጋት ውጤት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ ከማመንጨት እስከ ትግበራ በመምራትና በመሥራት ግንባር ቀደም ሆነው አሳይተውናልም ብለዋል። የጠራ እቅድ እና መዳረሻ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ ሀገራዊ ፕሮጀክት ከታዳጊ ህጻናት ጀምሮ የእድሜ በረከት እስከበዛላቸው አረጋውያን የተሳተፉበት ታሪካዊ የልማት ዘመቻ ሆኗል ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። የኢትዮጵያ ልጆች ለዓመታት በስኬት የተገበሩት ይህ ኢኒሼቲቭ ሀገራችንን በዓለም ፊት በክብር እያስጠራ ያለ የለውጥ ምልክት እስከመሆን ደርሷል ሲሉም አስታውቀዋል። እንደ ኮፕ 32 ያሉ ዓለም አቀፍ መድረኮችን የማስተናገድ እድሎችም በተባበረ ክንድ በተደመረ እሳቤ የመስራታችን ውጤቶች እና የብሔራዊ ዐሻራችን ሽልማቶች ናቸው ብለዋል። በአረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች የለውጥ ግቦቻችን የታዩ የትጋት ድል ፍሬዎች በተደመሩ ጥረቶች ኢትዮጵያ በእርግጥም እየለማች እየፈካች ትገኛለች ብለዋል። በሁሉም መስክ አቅደን የምንተገብራቸው ህልሞቻችን እስከሚሳኩ ድረስ በብርታት እንሠራለን ሲሉም ገልጸዋል በመልዕክታቸው። ‘ተስፋን እንትከል’ ሲሉም ሕብረተሰቡ በችግኝ ተከላ በንቃት እንዲሳተፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያን ጂኦ-ስትራቴጂክ ተጠቃሚነት ለማስጠበቅ የድንበርና የኤርፖርት ደኅንነቶችን ማዘመን ወሳኝ ጉዳይ ነው 
Jun 28, 2026 423
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያን ጂኦ-ስትራቴጂክ ተጠቃሚነት ለማስጠበቅ የድንበርና የኤርፖርት ደኅንነቶችን ማዘመን ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራልና የኤርፖርትና ድንበር አስተዳደር ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራም ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ። የተቀናጀ የኤርፖርት እና የድንበር አስተዳደር ትራንፎርሜሽን ፕሮግራም ላይ ያተኮረ የምክክርና የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራልና የኤርፖርትና ድንበር አስተዳደር ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራም ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በዚሁ ወቅት፤ የትራንስፎርሜሽን ፕሮግራሙ የኢትዮጵያን የደኅንነት ስጋቶች አስቀድሞ ለመከላከል፣ የሳይበር ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና በዲጂታል ዘመን ኢትዮጵያ ያላትን ተወዳዳሪነት ለማስቀጠል ወሳኝ ነው ብለዋል። ፕሮግራሙም ስጋቶችን በመረጃ አስደግፎ ለማወቅና ለመከላከል እንዲሁም በተቋማት መካከል የመረጃ ልውውጥን በማሳደግ ሽብርተኝነት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች፣ የገንዘብና የመሣሪያ ዝውውርን በጋራ ለመመከት አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ፕሮግራሙ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች እንዲለሙ በማድረግ የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥና አሰራሮች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲደገፉ ግብ የጣለ መሆኑንም አስረድተዋል። ለዚህም ስኬት የተዘጋጀው ፍኖተ-ካርታ የሚያስፈልጉትን የቴክኖሎጂ አቅም፣ የአሠራር ሥርዓቶች ስታንዳርድ፣ የሰው ሀብት፣ የመሠረተ-ልማት አቅርቦት እንዲሁም የሕግና የቁጥጥር ጉዳዮችን ለይቶ ማስቀመጡንም አብራርተዋል።   ፕሮግራሙ የሀገሪቱን የጂኦ-ስትራቴጂክ ቁመና ለማስጠበቅና የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አንዱ ማስፈጸሚያ መሣሪያ እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ጂኦ-ስትራቴጂክ ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የድንበርና የኤርፖርት ደኅንነቶችን ማዘመን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በዚህም ሀገሪቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ፍኖተ-ካርታው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ግቦችን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፣ ሀገሪቱ በቀጣይ ለምታስተናግደው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል። በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የጸጥታ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን ማጎልበት አለባቸው
Jun 28, 2026 443
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን ማጎልበት እንደሚገባቸው የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ ገለፁ። ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፣ከሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ እና ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር ለሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል። የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ፣ መልካም እሴቶች እንዲጎለብቱ እና ህዝቡ በክልሉ በሚከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የሚያደርገውን ተሳትፎ ማሳደግ ያስቻሉ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል። በተለይም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ፅንፈኛ ሀይሎች በማህበረሰቡ መካከል የሚነዙትን የጥላቻና ሀሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል አሰባሳቢና ገዢ ትርክቶች እንዲሰርጹ በማድረግ ረገድ አበረታች ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም አፍራሽ የሆኑ ፕሮፖጋንዳዎችን ቀድሞ በመከላከል የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅና ሕብረ ብሄራዊነት እንዲሰርፅና እንዲፀና በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች በክልሉ በሁሉም ዘርፎች ለተመዘገቡ ውጤቶች አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም አንስተዋል። በተጨማሪም የህዝብ ሰላምና አንድነት እንዲጎለብትና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አዎንታዊ ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል። የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናም በባለሙያዎቹ ዘንድ የሚታዩ ውስንነቶችን ለመቅረፍና ግንዛቤ ለማጎልበት ከፍተኛ እገዛ አለው ብለዋል። ተቋሙ ለህብረተሰቡ ወቅታዊ መረጃዎችን ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ለሚመለከታቸው አካላት መሰል ስልጠናዎች የመስጠት ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አቶ አለምሸት ተሾመ በበኩላቸው፥ ከዩኒቨርሲቲው የሚገኝ ዕውቀት የአካባቢውን ማህበረሰብና ተቋማት እንዲጠቅም በተለያዩ መንገዶች እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በሀረሪ ክልል ለሚገኙ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች የተሰጠው ስልጠናም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል። መደበኛ የሚባለው የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ መረጃዎቹ ተደራሽ የሚደረግላቸው ማህበረሰቦችን ነባራዊ ሁኔት በመለየት መልዕክቶችን ማስተላለፍ እንደሚገባ አቶ አለምሸት ገልፀዋል፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች መልዕክት በመቅረፅና የማስተላለፊያ ቴክኖሎጂዎች አጠቃቀም ላይ ራሳቸውን ሊያበቁ ይገባል ብለዋል። ሐረማያ ዩኒቨርሲቲም የባለሙያዎቹን አቅም ለመገንባት የበኩሉን አስተዋፅዖ እንደሚያበረክት ተናግረዋል። ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።
ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩ አጀንዳዎች የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት ያስችላሉ- የሀገር ሽማግሌዎች
Jun 28, 2026 543
ገንዳ ውኃ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩ አጀንዳዎች የቆዩ ችግሮችን በመፍታት ዘላቂ መፍትሄ የሚያመጡ መሆናቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውሀ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በየደረጃው ከሕዝብ ጋር ባካሄደው ተከታታይ ውይይት የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ ታሪካዊ ሂደት አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የምዕራብ ጎንደር ዞን የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተመረጡት አጀንዳዎች ተገቢና ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከሀገር ሽማግሌዎቹ መካከል በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውኃ ከተማ ነዋሪ አቶ ሰጠኝ ካሴ እንደገለጹት፣ ምክክሩ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባትና ለዘመናት ሳያግባቡ የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት መሰረት የሚጥል ነው። በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለጉባኤው የተለዩ አጀንዳዎች ለቆዩ አለመግባባቶች በመነጋገር ዘላቂ መፍትሄ ለማስቀመጥ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። የእስካሁኑ የምክክር ሂደት አካታችና ህዝቡ በየደረጃው ተወያይቶ ሃሳቡን በነጻነት እንዲገልጽና እንዲያንሸራሽር እድል የፈጠረ መሆኑንም የሀገር ሽማግሌው አቶ ሰጠኝ አውስተዋል። ይህም ለግጭት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በሰከነ የምክክር መድረክ በመፍታት ለሀገር ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥበትን አዲስ የውይይት ባህል ለመገንባት የራሱ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል። በሀገራዊ ምክክሩ የተለዩ አጀንዳዎች በቀጣይ የዜጎችን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት የሚያጠናክሩ እና በጋራ ሀገር የመገንባት ሂደትን የሚያፋጥኑ ናቸው ያሉት ደግሞ በዞኑ የነጋዴ ባህር ከተማ ነዋሪና የሀገር ሽማግሌ አቶ ዳገት ከፋለ ናቸው። ችግሮችን በውይይት መፍታት ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድና ፖለቲካዊ ልዩነቶች ለማጥበብ ድርሻው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ በቁርጠኝነት ከተሰራ መፍታት የማይቻል ችግር እንደማይኖር ማሳያ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የገንዳውኃ ከተማ ነዋሪና የሀገር ሽማግሌ ሼክ አደም ሱሌማን ናቸው። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚካሄደው ዋና የምክክር ጉበኤ በኮሚሽኑ የተለዩት አጀንዳዎች የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ ያገናዘቡና ለነበሩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄን ለመስጠት ትልቅ ተስፋ መሆናቸውን ተናግረዋል። በምክክሩ አለመግባባቶችን በውይይትና በይቅርታ በመሻገር የጋራ ሀገር ለመገንባት የሚደረገው ጥረት የሁሉንም ርብርብ ስለሚጠይቅ የድርሻቸውን እንደሚወጡም አክለዋል።
የሱማሌ ክልል ከለውጡ ወዲህ ያስመዘገበው ሁለንተናዊ የልማት ውጤት ሌሎች ክልሎችም በተሞክሮነት ሊወስዱት የሚገባ ነው
Jun 28, 2026 391
አዲስ አበባ፤ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የሱማሌ ክልል ከለውጡ ወዲህ በአጭር ጊዜ ያስመዘገበው ሁለንተናዊ የልማት ውጤት ሌሎች ክልሎችም በትልቅ ተሞክሮነት ሊወስዱት የሚገባ መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ገለጹ። ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ከሱማሌ ክልል ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከለውጡ በፊት በነበረው አግላይ የፖለቲካ ስርዓት የሱማሌ ክልል ከመሀል ፖለቲካ በመገለል የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ሳይሆን ቆይቷል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ የፈጠረው አካታችና አሳታፊ የፖለቲካ ምኅዳርም የሱማሌ ክልል ህዝብ ከነበረበት የሰላምና የልማት እጦት ተላቆ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጥበት ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል። የሱማሌ ክልል ህዝብ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ከሰላምና የልማት እጦት ተላቆ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ መሆኑን ገልጸዋል። የሱማሌ ክልል የመሰረተ ልማት ማስፋፊያና የግብርና ልማት ሥራዎችም በሀገራዊና ክልላዊ የልማት ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች እያስመዘገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በሱማሌ ክልል የተመዘገቡ የግብርና እና የመሰረተ ልማት ግንባታ ስኬቶች ክልሉን በአጭር ጊዜ ውስጥ የብልፅግና ተምሳሌት እያደረጉት መሆኑን ተናግረዋል። የጅግጅጋ ከተማ በፈጣን የልማትና የዕድገት ግስጋሴ ላይ ትገኛለች ያሉት ኃላፊው፤ ከተማዋም ከሀገር አልፎ ቀጣናዊ ኮንፈረንሶችን በማስተናገድ የቱሪዝም ማዕከል የሆነችበትን አቅም መፍጠሯን ገልጸዋል። የሱማሌ ክልል ከለውጡ ወዲህ በአጭር ጊዜ ያስመዘገበው ሁለንተናዊ የልማት ውጤት ሌሎች ክልሎችም በትልቅ ተሞክሮነት ሊወስዱት የሚገባ መሆኑን ጭምር አስገንዝበዋል። በቀጣይ የክልሉን የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል።
በጠቅላላ ምርጫው በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበር ማሸነፋቸው የዴሞክራሲ ምህዳሩን መስፋት ያረጋገጠ ነው 
Jun 28, 2026 569
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበር ማሸነፋቸው የዴሞክራሲ ምህዳሩን መስፋት ያረጋገጠ መሆኑን የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በክልል እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም የተሻለ የሀሳብ ብዝኃነት እንዲኖርና ጠንካራ የሆኑ የመንግሥት አካላትን የመገንባት ሂደትን ለማሳካት ያስችላል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በስኬት የተካሄደውን የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን ሲያገኝ በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። ከዚህም በተጨማሪ 10 ተፎካካሪ ፓርቲዎች እያንዳንዳቸው አንድ የምክር ቤት ወንበር አግኝተዋል። ለክልል ምክር ቤት ደግሞ ኢዜማ 73፣ ነእፓ 35፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 34፣ ኦብነግ 20፣ ጉህዴን 14፣ መድረክ 11፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 6፣ ሕዳሴ ፓርቲ 5 እና ቤህነን 5 አግኝተዋል። የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ ነቢሃ መሀመድ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ወንበሮችን ማሸነፋቸው የፖለቲካ ምህዳሩ እየሰፋ መሆኑን ያሳያል። በፓርላማም ሆነ በክልል የሕዝብ ምክር ቤቶች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ግብዓት የሚሆኑ ሐሳቦችን በማቅረብ ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጠናከር የላቀ አበርክቶ እንዲኖራቸው ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። ሀገር የሚገነባው በጋራ ነው ያሉት ኃላፊዋ፤ ፓርቲዎች በርከት ባለ ቁጥር ወደ ሕዝብ ምክር ቤቶች መግባታቸው ብዝሃነት ያለው ሐሳብ እንዲስተናገድ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርም አብራርተዋል። በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች በጋራ ለመሥራት አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል ያሉት ወይዘሮ ነቢሃ፤ ለተቋማት ግንባታ መሳለጥ ትልቅ ምዕራፍ ከፋች ነው ሲሉ ተናግረዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ድምፅ መንግሥት ለመመስረት ብቸኛው መንገድ መሆኑን ያመላከተ መሆኑን ጠቅሰው፤ መንግሥት የሚመሰረተው በኃይል ሳይሆን በሐሳብ ብቻ መሆኑን ትምህርት የሰጠ ነው ብለዋል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ከምስረታው ጀምሮ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ በቀጣይም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሀገር ሉዓላዊነት መከበር ዙሪያ መንግሥት ከሚመሰርተው ብልጽግና ፓርቲ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራትም ውጤታማ እንዲሆኑ ፓርቲው የሚጠበቅበትን ድርሻ እንደሚወጣም አስረድተዋል። የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ወዴፓ) ፕሬዝዳንት አቶ ነጻነት ጣሰው በበኩላቸው፤ ፓርቲዎች በሀገራዊ ጉዳይ የላቀ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የማድረግ በጎ ጅምር ሊጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል። እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ተቀራርቦ መሥራት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን መፍጠር ሀገር ለማሻገር ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ፣ በዚህ ረገድ ይበልጥ ሊሰራ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ መጠናከር የበኩሉን ኃላፊነት ለመወጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አመልክተዋል። ለዚህም በተለያዩ መስኮች ለሀገር ግንባታ አበርክቶ ያላቸው የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን በጥናት ለይቶ ለማቅረብ ያልተቆጠበ ጥረት እንደሚያደርግም ጠቁመዋል። ለሀገረ መንግሥት ግንባታ መሳካት ቁልፍ መንገድ ምክክር ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ሀገራዊ ምክክሩ የታለመለትን ግብ እንዲያሳካ ፓርቲው የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንደሚወጣም አረጋግጠዋል።
የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማህበረሰቡ የሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም አምባሳደር መሆን አለባቸው -የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን
Jun 27, 2026 1717
ቢሻን ጉራቻ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ):- የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማህበረሰቡ የሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በማህበረሰቡ ውስጥ የለውጥ ፋና ወጊ እና የሰላም አምባሳደር መሆን እንዳለባቸው የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስገነዘበ። በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩና የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉም ተገልጿል።   ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች በቢሻን ጉራቻ ማዕከል የወሰዱትን የተሃድሶ ስልጠና አጠናቀው ወደ ማህበረሰቡ የመቀላቀል መርሃ ግብር አካሂዷል። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን በመርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ መደበኛ ህይወት እየተመለሱ ነው። ከህዳር 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ በተለያዩ ክልሎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩና የሰላም አማራጭን የተቀበሉ በርካታ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለሳቸውን ገልጸዋል። የዛሬዎቹን ጨምሮ በኦሮሚያ ክልልም የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ መቀላቀላቸውን ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል። የክልሉ መንግስት የቀድሞ ታጣቂዎች በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተሰማርተው ውጤታማ እንዲሆኑ የወሰደውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። በዛሬው ዕለት ስልጠናውን አጠናቀው ወደ ማህበረሰቡ የሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በማህበረሰቡ ውስጥ የለውጥ ፋና ወጊ እና የሰላም አምባሳደር መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ኤባ ገርባ በበኩላቸው፤ የሰላም አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በዘላቂነት ህይወታቸውን እንዲመሩ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም የሰላም አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም በ265 ኢንተርፕራይዞች በማደራጀት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በዛሬው ዕለት የተሃድሶ ስልጠና ያጠናቀቁትንም በቀጣይ ህይወታቸውን በዘላቂነት የሚመሩበትን ሂደት የማመቻቸት ስራ መሰራቱንና የሚደረገው ክትትልና ድጋፍ እንደሚጠናከር አስረድተዋል። ከባሌ አካባቢ የመጣውና በተሃድሶ ስልጠና ውስጥ ያለፈው አብድራዛቅ ነገዎ፤ በተሳሳተ መረጃ በጫካ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን ተናግሯል። "ለኦሮሞ እንታገላለን ብለን ህዝቡን ለከፋ አደጋ ነው የዳረግነው" ያለው የቀድሞው ታጣቂ ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የበደለውን ህዝብ ለመካስ መዘጋጀቱን ገልጿል። በመርሃ ግብሩ ላይ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አመራሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ አባገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።
ኮሚሽኑ ለውይይት ያቀረባቸው አጀንዳዎች ሰላምና አብሮነትን የሚያጠናክሩ ናቸው- ምሁራን
Jun 27, 2026 1143
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለውይይት ያቀረባቸው አጀንዳዎች መሠረታዊ ችግሮች ነቅሶ በማውጣት ሰላምና አብሮነትን የሚያጠናክሩ መሆናቸውን ምሁራን ተናገሩ፡፡ ኮሚሽኑ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ ለሚካሄደው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ የሚቀርቡ 8 አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ይህንን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁት፤ ኮሚሽኑ ይፋ ያደረጋቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች ከዚህ ቀደም የነበሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት የሚያስችሉ ሐሳቦችን የያዙ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚሀም በኮሚሽኑ ለውይይት የቀረቡ አጀንዳዎች የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች ነቅሶ በማውጣት ሰላምና አብሮነትን የሚያጠናክሩ ናቸው ሲሉም አክለዋል። በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንዳሉት የፖለቲካ ሥርዓቱን ከኃይል እሳቤ ለምክክር ወደ መድረክ ማምጣት መቻል ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት ነው። ኮሚሽኑ ለይቶ ያቀረባቸው አጀንዳዎች የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች ነቅሶ በማውጣት ሰላምና አብሮነትን የሚያጎለብቱ መፍትሔዎችን የሚያመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ''ለራሳችን ችግሮች በራሳችን መፍትሔ ለማምጣት በጠረጴዛ ዙሪያ የመቀመጥ ዕድል መፈጠሩ ለኢትዮጵያ ወሳኝ የታሪክ በርን የሚከፍትና ወደፊትም በትውልድ የሚወሳ የታሪክ አካል ይሆናል'' ብለዋል። ለውይይት የቀረቡት ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች በንዑስ አጀንዳነት በርካታ ዝርዝር ጉዳዮችን እንደሚያነሱ ገልጸው ኮሚሽኑ የአካታችነትን መርህ ተግባራዊ በማድረግ ምክክሩን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ማድረሱ ትልቅ ተቋማዊ ስኬት እንደሆነም አክለዋል። ከዚህ ቀደም ይህ ሥርዓት ባለመሞከሩ ብዙ ስብራቶች ገጥመውናል ያሉት ተመራማሪው በብዙ ድካምና ትዕግስት የተፈጠረው የምክክር መድረክ "የሥነ ልቦናና የሞራል ከፍታችን ማረጋገጫ ነው" ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በርሁን በሀገራችን በፖለቲካ እና ሌሎች ምክንያቶች የተፈጠሩ መሠረታዊ ችግሮችን ለመፍታት የተለዩ አጀንዳዎችን በአግባቡ ወደ ውጤት መቀየር ከሁሉም ዜጋ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል። ወደ ምክክር መድረክ የመጡትን የተቋም ግንባታ፣ የሕግ የበላይነት እና ሌሎች ጉዳዮች በውይይት ቋሚ መሠረት ማስያዝ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በተጠናከረ ሁኔታ ለማስኬድ ያስችላል ብለዋል።  
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የለያቸው አጀንዳዎች የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ሀሳብ ያካተቱ ናቸው
Jun 27, 2026 1150
ሮቤ፣ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የለያቸው አጀንዳዎች መሰረታዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉና አካታች መሆናቸውን የሮቤ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። ኮሚሽኑ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ማካሄድ ለሚጀምረው ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን መለየቱ ይታወሳል። በኮሚሽኑ የተለዩትን አጀንዳዎች በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሮቤ ከተማ ነዋሪዎችና የሥራ ኃላፊዎች፤ የተመረጡት አጀንዳዎች የሀገሪቱን መሰረታዊ ችግሮች ለመፍታት የሚያስችሉና ሁሉንም አካታች ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የዋቆ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደሳለኝ አብደታ፤ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በሀገሪቱ የነበሩ አለመግባባቶችን መፍታት ያስችላል ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም በምክክር ኮሚሽኑ የተለዩት ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች የኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች ለመፍታት የሚያስችሉና አካታች በመሆናቸው፣ ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። የባሌ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባልደረባ አቶ አበባ ገላልቻ በበኩላቸው፤ ኮሚሽኑ አጀንዳዎችን ሰብስቦ አካታች በሆነ መልኩ ለምክክር ያቀረበበት መንገድ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለምክክር ሂደቱ ውጤታማነት በተለያዩ መድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር የዜግነት ግዴታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። መምህር ጸጋዬ በየና በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ በተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች መካከል የሚስተዋሉ ችግሮችን በውይይት ፈትቶ አብሮነትን ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን የፈጠረ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሂደት የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች በምክክር ለመፍታት የሚያስችል ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን በመረዳት፣ ለውጤታማነቱ ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ አመልክተዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ገረመው ከፍያለሁ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ሀሳብ በመቀበል መሰረታዊና ወሳኝ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የለያቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች አካታችና ከዚህ በፊት የነበሩ ቁርሾዎች እንዲፈቱ ዕድል የሚፈጥሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። አስተያየት ሰጪዎቹ አክለውም፣ የኮሚሽኑ የእስከ አሁኑ ሂደት የሀሳብ ፍትሃዊነትና አካታችነት የሰፈነበት መሆኑን በመረዳት ለውጤታማነቱ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ከለውጡ በኋላ የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ለልማት ስኬት ፅኑ መሰረት እየሆነ ነው
Jun 27, 2026 1144
ሃዋሳ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ):- ከለውጡ በኋላ የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ለልማት ስኬት ጽኑ መሰረት መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ የተዘጋጀው የውይይት መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል።   በመድረኩ የተገኙት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድርሻቸውን ተወጥተዋል ብለዋል። የሲዳማ ክልል ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ያደረጉት ቅንጅታዊ ስራ ለምርጫው ስኬት ጉልህ ድርሻ ነበረው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ አጠቃላይ ህዝቡም ለሰላምና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያሳየውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ለልማት ስኬት ፅኑ መሰረት መሆኑን ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ በለጠ ሲጌቦ፤ በተፈጠረው ምቹ እና አሳታፊ የፖለቲካ ምህዳር በክልሉ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ለምርጫው ስኬት የጋራ ምክር ቤቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራቱን ጠቅሰው የዛሬው መድረክ ዋና አላማም ለስኬቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላትን እውቅና መስጠት ነው ብለዋል። በክልሉ የሚንቀሳቀሱ 24 የፖለቲካ ፓርቲዎች አብላጫ መቀመጫ በማግኘቱ መንግስት ከሚመሰርተው ብልጽግና ፓርቲ ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራና በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ኤርሚያስ፤ በክልሉ የተፈጠረው ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገረ መንግስት ግንባታው ሚናቸውን እንዲወጡ ማስቻሉን ገልጸዋል። ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጋራ ምክር ቤቱ የበኩሉን ድርሻ ማበርከቱን ጠቅሰው በቀጣይም ከመንግስት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ ነን ብለዋል። በመድረኩ የጋራ ምክር ቤቱ በቅድመ ምርጫ በምርጫ እለትና በድህረ ምርጫ ባከናወናቸው ተግባራት ላይ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን ለምርጫው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።
ፖለቲካ
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን ማጎልበት አለባቸው
Jun 28, 2026 443
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን ማጎልበት እንደሚገባቸው የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ ገለፁ። ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፣ከሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ እና ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር ለሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል። የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ፣ መልካም እሴቶች እንዲጎለብቱ እና ህዝቡ በክልሉ በሚከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የሚያደርገውን ተሳትፎ ማሳደግ ያስቻሉ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል። በተለይም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ፅንፈኛ ሀይሎች በማህበረሰቡ መካከል የሚነዙትን የጥላቻና ሀሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል አሰባሳቢና ገዢ ትርክቶች እንዲሰርጹ በማድረግ ረገድ አበረታች ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም አፍራሽ የሆኑ ፕሮፖጋንዳዎችን ቀድሞ በመከላከል የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅና ሕብረ ብሄራዊነት እንዲሰርፅና እንዲፀና በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች በክልሉ በሁሉም ዘርፎች ለተመዘገቡ ውጤቶች አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም አንስተዋል። በተጨማሪም የህዝብ ሰላምና አንድነት እንዲጎለብትና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አዎንታዊ ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል። የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናም በባለሙያዎቹ ዘንድ የሚታዩ ውስንነቶችን ለመቅረፍና ግንዛቤ ለማጎልበት ከፍተኛ እገዛ አለው ብለዋል። ተቋሙ ለህብረተሰቡ ወቅታዊ መረጃዎችን ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ለሚመለከታቸው አካላት መሰል ስልጠናዎች የመስጠት ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አቶ አለምሸት ተሾመ በበኩላቸው፥ ከዩኒቨርሲቲው የሚገኝ ዕውቀት የአካባቢውን ማህበረሰብና ተቋማት እንዲጠቅም በተለያዩ መንገዶች እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በሀረሪ ክልል ለሚገኙ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች የተሰጠው ስልጠናም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል። መደበኛ የሚባለው የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ መረጃዎቹ ተደራሽ የሚደረግላቸው ማህበረሰቦችን ነባራዊ ሁኔት በመለየት መልዕክቶችን ማስተላለፍ እንደሚገባ አቶ አለምሸት ገልፀዋል፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች መልዕክት በመቅረፅና የማስተላለፊያ ቴክኖሎጂዎች አጠቃቀም ላይ ራሳቸውን ሊያበቁ ይገባል ብለዋል። ሐረማያ ዩኒቨርሲቲም የባለሙያዎቹን አቅም ለመገንባት የበኩሉን አስተዋፅዖ እንደሚያበረክት ተናግረዋል። ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።
ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩ አጀንዳዎች የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት ያስችላሉ- የሀገር ሽማግሌዎች
Jun 28, 2026 543
ገንዳ ውኃ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩ አጀንዳዎች የቆዩ ችግሮችን በመፍታት ዘላቂ መፍትሄ የሚያመጡ መሆናቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውሀ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በየደረጃው ከሕዝብ ጋር ባካሄደው ተከታታይ ውይይት የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ ታሪካዊ ሂደት አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የምዕራብ ጎንደር ዞን የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተመረጡት አጀንዳዎች ተገቢና ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከሀገር ሽማግሌዎቹ መካከል በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውኃ ከተማ ነዋሪ አቶ ሰጠኝ ካሴ እንደገለጹት፣ ምክክሩ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባትና ለዘመናት ሳያግባቡ የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት መሰረት የሚጥል ነው። በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለጉባኤው የተለዩ አጀንዳዎች ለቆዩ አለመግባባቶች በመነጋገር ዘላቂ መፍትሄ ለማስቀመጥ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። የእስካሁኑ የምክክር ሂደት አካታችና ህዝቡ በየደረጃው ተወያይቶ ሃሳቡን በነጻነት እንዲገልጽና እንዲያንሸራሽር እድል የፈጠረ መሆኑንም የሀገር ሽማግሌው አቶ ሰጠኝ አውስተዋል። ይህም ለግጭት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በሰከነ የምክክር መድረክ በመፍታት ለሀገር ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥበትን አዲስ የውይይት ባህል ለመገንባት የራሱ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል። በሀገራዊ ምክክሩ የተለዩ አጀንዳዎች በቀጣይ የዜጎችን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት የሚያጠናክሩ እና በጋራ ሀገር የመገንባት ሂደትን የሚያፋጥኑ ናቸው ያሉት ደግሞ በዞኑ የነጋዴ ባህር ከተማ ነዋሪና የሀገር ሽማግሌ አቶ ዳገት ከፋለ ናቸው። ችግሮችን በውይይት መፍታት ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድና ፖለቲካዊ ልዩነቶች ለማጥበብ ድርሻው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ በቁርጠኝነት ከተሰራ መፍታት የማይቻል ችግር እንደማይኖር ማሳያ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የገንዳውኃ ከተማ ነዋሪና የሀገር ሽማግሌ ሼክ አደም ሱሌማን ናቸው። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚካሄደው ዋና የምክክር ጉበኤ በኮሚሽኑ የተለዩት አጀንዳዎች የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ ያገናዘቡና ለነበሩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄን ለመስጠት ትልቅ ተስፋ መሆናቸውን ተናግረዋል። በምክክሩ አለመግባባቶችን በውይይትና በይቅርታ በመሻገር የጋራ ሀገር ለመገንባት የሚደረገው ጥረት የሁሉንም ርብርብ ስለሚጠይቅ የድርሻቸውን እንደሚወጡም አክለዋል።
የሱማሌ ክልል ከለውጡ ወዲህ ያስመዘገበው ሁለንተናዊ የልማት ውጤት ሌሎች ክልሎችም በተሞክሮነት ሊወስዱት የሚገባ ነው
Jun 28, 2026 391
አዲስ አበባ፤ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የሱማሌ ክልል ከለውጡ ወዲህ በአጭር ጊዜ ያስመዘገበው ሁለንተናዊ የልማት ውጤት ሌሎች ክልሎችም በትልቅ ተሞክሮነት ሊወስዱት የሚገባ መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ገለጹ። ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ከሱማሌ ክልል ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከለውጡ በፊት በነበረው አግላይ የፖለቲካ ስርዓት የሱማሌ ክልል ከመሀል ፖለቲካ በመገለል የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ሳይሆን ቆይቷል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ የፈጠረው አካታችና አሳታፊ የፖለቲካ ምኅዳርም የሱማሌ ክልል ህዝብ ከነበረበት የሰላምና የልማት እጦት ተላቆ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጥበት ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል። የሱማሌ ክልል ህዝብ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ከሰላምና የልማት እጦት ተላቆ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ መሆኑን ገልጸዋል። የሱማሌ ክልል የመሰረተ ልማት ማስፋፊያና የግብርና ልማት ሥራዎችም በሀገራዊና ክልላዊ የልማት ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች እያስመዘገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በሱማሌ ክልል የተመዘገቡ የግብርና እና የመሰረተ ልማት ግንባታ ስኬቶች ክልሉን በአጭር ጊዜ ውስጥ የብልፅግና ተምሳሌት እያደረጉት መሆኑን ተናግረዋል። የጅግጅጋ ከተማ በፈጣን የልማትና የዕድገት ግስጋሴ ላይ ትገኛለች ያሉት ኃላፊው፤ ከተማዋም ከሀገር አልፎ ቀጣናዊ ኮንፈረንሶችን በማስተናገድ የቱሪዝም ማዕከል የሆነችበትን አቅም መፍጠሯን ገልጸዋል። የሱማሌ ክልል ከለውጡ ወዲህ በአጭር ጊዜ ያስመዘገበው ሁለንተናዊ የልማት ውጤት ሌሎች ክልሎችም በትልቅ ተሞክሮነት ሊወስዱት የሚገባ መሆኑን ጭምር አስገንዝበዋል። በቀጣይ የክልሉን የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል።
በጠቅላላ ምርጫው በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበር ማሸነፋቸው የዴሞክራሲ ምህዳሩን መስፋት ያረጋገጠ ነው 
Jun 28, 2026 569
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበር ማሸነፋቸው የዴሞክራሲ ምህዳሩን መስፋት ያረጋገጠ መሆኑን የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በክልል እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም የተሻለ የሀሳብ ብዝኃነት እንዲኖርና ጠንካራ የሆኑ የመንግሥት አካላትን የመገንባት ሂደትን ለማሳካት ያስችላል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በስኬት የተካሄደውን የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን ሲያገኝ በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። ከዚህም በተጨማሪ 10 ተፎካካሪ ፓርቲዎች እያንዳንዳቸው አንድ የምክር ቤት ወንበር አግኝተዋል። ለክልል ምክር ቤት ደግሞ ኢዜማ 73፣ ነእፓ 35፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 34፣ ኦብነግ 20፣ ጉህዴን 14፣ መድረክ 11፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 6፣ ሕዳሴ ፓርቲ 5 እና ቤህነን 5 አግኝተዋል። የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ ነቢሃ መሀመድ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ወንበሮችን ማሸነፋቸው የፖለቲካ ምህዳሩ እየሰፋ መሆኑን ያሳያል። በፓርላማም ሆነ በክልል የሕዝብ ምክር ቤቶች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ግብዓት የሚሆኑ ሐሳቦችን በማቅረብ ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጠናከር የላቀ አበርክቶ እንዲኖራቸው ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። ሀገር የሚገነባው በጋራ ነው ያሉት ኃላፊዋ፤ ፓርቲዎች በርከት ባለ ቁጥር ወደ ሕዝብ ምክር ቤቶች መግባታቸው ብዝሃነት ያለው ሐሳብ እንዲስተናገድ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርም አብራርተዋል። በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች በጋራ ለመሥራት አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል ያሉት ወይዘሮ ነቢሃ፤ ለተቋማት ግንባታ መሳለጥ ትልቅ ምዕራፍ ከፋች ነው ሲሉ ተናግረዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ድምፅ መንግሥት ለመመስረት ብቸኛው መንገድ መሆኑን ያመላከተ መሆኑን ጠቅሰው፤ መንግሥት የሚመሰረተው በኃይል ሳይሆን በሐሳብ ብቻ መሆኑን ትምህርት የሰጠ ነው ብለዋል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ከምስረታው ጀምሮ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ በቀጣይም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሀገር ሉዓላዊነት መከበር ዙሪያ መንግሥት ከሚመሰርተው ብልጽግና ፓርቲ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራትም ውጤታማ እንዲሆኑ ፓርቲው የሚጠበቅበትን ድርሻ እንደሚወጣም አስረድተዋል። የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ወዴፓ) ፕሬዝዳንት አቶ ነጻነት ጣሰው በበኩላቸው፤ ፓርቲዎች በሀገራዊ ጉዳይ የላቀ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የማድረግ በጎ ጅምር ሊጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል። እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ተቀራርቦ መሥራት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን መፍጠር ሀገር ለማሻገር ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ፣ በዚህ ረገድ ይበልጥ ሊሰራ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ መጠናከር የበኩሉን ኃላፊነት ለመወጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አመልክተዋል። ለዚህም በተለያዩ መስኮች ለሀገር ግንባታ አበርክቶ ያላቸው የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን በጥናት ለይቶ ለማቅረብ ያልተቆጠበ ጥረት እንደሚያደርግም ጠቁመዋል። ለሀገረ መንግሥት ግንባታ መሳካት ቁልፍ መንገድ ምክክር ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ሀገራዊ ምክክሩ የታለመለትን ግብ እንዲያሳካ ፓርቲው የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንደሚወጣም አረጋግጠዋል።
የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማህበረሰቡ የሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም አምባሳደር መሆን አለባቸው -የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን
Jun 27, 2026 1717
ቢሻን ጉራቻ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ):- የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማህበረሰቡ የሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በማህበረሰቡ ውስጥ የለውጥ ፋና ወጊ እና የሰላም አምባሳደር መሆን እንዳለባቸው የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስገነዘበ። በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩና የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉም ተገልጿል።   ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች በቢሻን ጉራቻ ማዕከል የወሰዱትን የተሃድሶ ስልጠና አጠናቀው ወደ ማህበረሰቡ የመቀላቀል መርሃ ግብር አካሂዷል። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን በመርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ መደበኛ ህይወት እየተመለሱ ነው። ከህዳር 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ በተለያዩ ክልሎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩና የሰላም አማራጭን የተቀበሉ በርካታ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለሳቸውን ገልጸዋል። የዛሬዎቹን ጨምሮ በኦሮሚያ ክልልም የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ መቀላቀላቸውን ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል። የክልሉ መንግስት የቀድሞ ታጣቂዎች በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተሰማርተው ውጤታማ እንዲሆኑ የወሰደውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። በዛሬው ዕለት ስልጠናውን አጠናቀው ወደ ማህበረሰቡ የሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በማህበረሰቡ ውስጥ የለውጥ ፋና ወጊ እና የሰላም አምባሳደር መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ኤባ ገርባ በበኩላቸው፤ የሰላም አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በዘላቂነት ህይወታቸውን እንዲመሩ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም የሰላም አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም በ265 ኢንተርፕራይዞች በማደራጀት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በዛሬው ዕለት የተሃድሶ ስልጠና ያጠናቀቁትንም በቀጣይ ህይወታቸውን በዘላቂነት የሚመሩበትን ሂደት የማመቻቸት ስራ መሰራቱንና የሚደረገው ክትትልና ድጋፍ እንደሚጠናከር አስረድተዋል። ከባሌ አካባቢ የመጣውና በተሃድሶ ስልጠና ውስጥ ያለፈው አብድራዛቅ ነገዎ፤ በተሳሳተ መረጃ በጫካ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን ተናግሯል። "ለኦሮሞ እንታገላለን ብለን ህዝቡን ለከፋ አደጋ ነው የዳረግነው" ያለው የቀድሞው ታጣቂ ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የበደለውን ህዝብ ለመካስ መዘጋጀቱን ገልጿል። በመርሃ ግብሩ ላይ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አመራሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ አባገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።
ኮሚሽኑ ለውይይት ያቀረባቸው አጀንዳዎች ሰላምና አብሮነትን የሚያጠናክሩ ናቸው- ምሁራን
Jun 27, 2026 1143
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለውይይት ያቀረባቸው አጀንዳዎች መሠረታዊ ችግሮች ነቅሶ በማውጣት ሰላምና አብሮነትን የሚያጠናክሩ መሆናቸውን ምሁራን ተናገሩ፡፡ ኮሚሽኑ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ ለሚካሄደው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ የሚቀርቡ 8 አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ይህንን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁት፤ ኮሚሽኑ ይፋ ያደረጋቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች ከዚህ ቀደም የነበሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት የሚያስችሉ ሐሳቦችን የያዙ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚሀም በኮሚሽኑ ለውይይት የቀረቡ አጀንዳዎች የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች ነቅሶ በማውጣት ሰላምና አብሮነትን የሚያጠናክሩ ናቸው ሲሉም አክለዋል። በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንዳሉት የፖለቲካ ሥርዓቱን ከኃይል እሳቤ ለምክክር ወደ መድረክ ማምጣት መቻል ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት ነው። ኮሚሽኑ ለይቶ ያቀረባቸው አጀንዳዎች የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች ነቅሶ በማውጣት ሰላምና አብሮነትን የሚያጎለብቱ መፍትሔዎችን የሚያመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ''ለራሳችን ችግሮች በራሳችን መፍትሔ ለማምጣት በጠረጴዛ ዙሪያ የመቀመጥ ዕድል መፈጠሩ ለኢትዮጵያ ወሳኝ የታሪክ በርን የሚከፍትና ወደፊትም በትውልድ የሚወሳ የታሪክ አካል ይሆናል'' ብለዋል። ለውይይት የቀረቡት ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች በንዑስ አጀንዳነት በርካታ ዝርዝር ጉዳዮችን እንደሚያነሱ ገልጸው ኮሚሽኑ የአካታችነትን መርህ ተግባራዊ በማድረግ ምክክሩን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ማድረሱ ትልቅ ተቋማዊ ስኬት እንደሆነም አክለዋል። ከዚህ ቀደም ይህ ሥርዓት ባለመሞከሩ ብዙ ስብራቶች ገጥመውናል ያሉት ተመራማሪው በብዙ ድካምና ትዕግስት የተፈጠረው የምክክር መድረክ "የሥነ ልቦናና የሞራል ከፍታችን ማረጋገጫ ነው" ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በርሁን በሀገራችን በፖለቲካ እና ሌሎች ምክንያቶች የተፈጠሩ መሠረታዊ ችግሮችን ለመፍታት የተለዩ አጀንዳዎችን በአግባቡ ወደ ውጤት መቀየር ከሁሉም ዜጋ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል። ወደ ምክክር መድረክ የመጡትን የተቋም ግንባታ፣ የሕግ የበላይነት እና ሌሎች ጉዳዮች በውይይት ቋሚ መሠረት ማስያዝ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በተጠናከረ ሁኔታ ለማስኬድ ያስችላል ብለዋል።  
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የለያቸው አጀንዳዎች የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ሀሳብ ያካተቱ ናቸው
Jun 27, 2026 1150
ሮቤ፣ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የለያቸው አጀንዳዎች መሰረታዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉና አካታች መሆናቸውን የሮቤ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። ኮሚሽኑ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ማካሄድ ለሚጀምረው ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን መለየቱ ይታወሳል። በኮሚሽኑ የተለዩትን አጀንዳዎች በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሮቤ ከተማ ነዋሪዎችና የሥራ ኃላፊዎች፤ የተመረጡት አጀንዳዎች የሀገሪቱን መሰረታዊ ችግሮች ለመፍታት የሚያስችሉና ሁሉንም አካታች ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የዋቆ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደሳለኝ አብደታ፤ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በሀገሪቱ የነበሩ አለመግባባቶችን መፍታት ያስችላል ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም በምክክር ኮሚሽኑ የተለዩት ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች የኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች ለመፍታት የሚያስችሉና አካታች በመሆናቸው፣ ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። የባሌ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባልደረባ አቶ አበባ ገላልቻ በበኩላቸው፤ ኮሚሽኑ አጀንዳዎችን ሰብስቦ አካታች በሆነ መልኩ ለምክክር ያቀረበበት መንገድ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለምክክር ሂደቱ ውጤታማነት በተለያዩ መድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር የዜግነት ግዴታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። መምህር ጸጋዬ በየና በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ በተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች መካከል የሚስተዋሉ ችግሮችን በውይይት ፈትቶ አብሮነትን ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን የፈጠረ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሂደት የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች በምክክር ለመፍታት የሚያስችል ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን በመረዳት፣ ለውጤታማነቱ ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ አመልክተዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ገረመው ከፍያለሁ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ሀሳብ በመቀበል መሰረታዊና ወሳኝ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የለያቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች አካታችና ከዚህ በፊት የነበሩ ቁርሾዎች እንዲፈቱ ዕድል የሚፈጥሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። አስተያየት ሰጪዎቹ አክለውም፣ የኮሚሽኑ የእስከ አሁኑ ሂደት የሀሳብ ፍትሃዊነትና አካታችነት የሰፈነበት መሆኑን በመረዳት ለውጤታማነቱ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ከለውጡ በኋላ የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ለልማት ስኬት ፅኑ መሰረት እየሆነ ነው
Jun 27, 2026 1144
ሃዋሳ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ):- ከለውጡ በኋላ የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ለልማት ስኬት ጽኑ መሰረት መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ የተዘጋጀው የውይይት መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል።   በመድረኩ የተገኙት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድርሻቸውን ተወጥተዋል ብለዋል። የሲዳማ ክልል ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ያደረጉት ቅንጅታዊ ስራ ለምርጫው ስኬት ጉልህ ድርሻ ነበረው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ አጠቃላይ ህዝቡም ለሰላምና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያሳየውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ለልማት ስኬት ፅኑ መሰረት መሆኑን ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ በለጠ ሲጌቦ፤ በተፈጠረው ምቹ እና አሳታፊ የፖለቲካ ምህዳር በክልሉ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ለምርጫው ስኬት የጋራ ምክር ቤቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራቱን ጠቅሰው የዛሬው መድረክ ዋና አላማም ለስኬቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላትን እውቅና መስጠት ነው ብለዋል። በክልሉ የሚንቀሳቀሱ 24 የፖለቲካ ፓርቲዎች አብላጫ መቀመጫ በማግኘቱ መንግስት ከሚመሰርተው ብልጽግና ፓርቲ ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራና በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ኤርሚያስ፤ በክልሉ የተፈጠረው ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገረ መንግስት ግንባታው ሚናቸውን እንዲወጡ ማስቻሉን ገልጸዋል። ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጋራ ምክር ቤቱ የበኩሉን ድርሻ ማበርከቱን ጠቅሰው በቀጣይም ከመንግስት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ ነን ብለዋል። በመድረኩ የጋራ ምክር ቤቱ በቅድመ ምርጫ በምርጫ እለትና በድህረ ምርጫ ባከናወናቸው ተግባራት ላይ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን ለምርጫው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።
ማህበራዊ
መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አካዳሚያዊ ነፃነት የሚያጎናጽፍ የራስ ገዝ አስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋት ምቹ ዕድል ፈጥሯል 
Jun 28, 2026 291
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አካዳሚያዊ ነፃነት የሚያጎናጽፍ የራስ ገዝ አስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋት ምቹ ዕድል መፍጠሩን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስክና ደረጃዎች ያሰለጠናቸውን 2 ሺ 882 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡   በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ (ዶ/ር)፣ የዩንቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተሾመ ነቃጥበብ(ዶ/ር)፣ የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ አባላትና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ (ዶ/ር) በሥነ-ሥርዓቱ እንደገለጹት፤ መንግስት እየሰራቸው ካሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል በትምህርት ዘርፉ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል። በዚህም መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አካዳሚያዊ ነፃነት የሚያጎናጽፍ የራስ ገዝ አስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋት ምቹ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ምሩቃኑ በተመረቁበት የትምህርት መስክ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በታማኝነትና ቅንነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋልም ብለዋል። በቀጣይም ተመራቂዎች ራሳቸውን በእውቀት በማብቃት በሀገራቸው የልማት ስራ ንቁ ተሳታፊ በመሆን የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ተሾመ ነቃጥበብ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዛሬ ተመራቂዎች እዚህ መድረስ የብዙ ድካም እና ጥረት ውጤት መሆኑን ገልፀው የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።   ዩኒቨርሲቲው ስር ሰዶ የቆየውን የትምህርት ጥራት እድገት ጉድለትን ለመፍታት ሙሉ ትኩረቱ ሰጥቶ በሰራቸው ስራዎች ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ዩኒቨርሲቲው ከሀገር ውስጥና ከጎረቤት ሀገራት ጭምር ተማሪዎችን በመቀበል ጥራት ያለው ትምህርት በመስጠት በርካታ ምሁራንን እያፈራ መሆኑን ገልጸዋል። በዩንቨርሲቲው የፊዚክስ ትምህርት ክፍል ከፍተኛ የማዕረግ ተመራቂ ኤርሚያስ አወቀ፤ በትጋት በማጥናት ለቀጣይ ህይወቱ ስንቅ የሚሆን ከፍተኛ የትምህርት ውጤት አምጥቶ ለምርቃት መብቃቱ እንዳስደሰተው ገልጿል።   ሌላኛዋ ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል 3 ነጥብ 81 በማስመዝገብ ከፍተኛ ውጤት ምሩቅ ሰላማዊት አበራ፤ የቤተሰብ ኃላፊነትን ከትምህርት ጋር በማጣመር ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባ በመመረቋ ኩራት እንደሚሰማት ተናግራለች።   የአካውንቲንግና ፋይናንስ ትምህርት ክፍል 3 ነጥብ 99 በማምጣት የማዕረግና የሜዳሊያ ተሸላሚው ሀለፎም አብርሀ በበኩሉ፤ የመምህራን እገዛና ጊዜውን በአግባቡ መጠቀሙ በከፍተኛ ውጤት ለመመረቅ መብቃቱን አንስቷል።   በቀጣይም በትምህርት ቆይታቸው የሸመቱትን ዕውቀትና ክህሎት ህዝባቸውንና ሀገራቸውን በታማኝነት ለማገልገል እንደሚጠቀሙበት ምሩቃኑ አረጋግጠዋል።
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 565
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
 በክልሉ የፍትህ ሪፎርሙን በማሳካት አገልግሎቱን ቀልጣፋ ለማድረግ ለሰው ሀይል ልማት ትኩረት ተሰጥቷል 
Jun 28, 2026 255
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የፍትህ ሪፎርሙን በማሳካት አገልግሎቱን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ለሰው ሀይል ልማት ትኩረት መሰጠቱን የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቢሮ ገለጸ ። የኦሮሚያ ህግ ምርምርና ፍትህ ኢንስቲትዩት ለ5ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ረዳት ዳኞችና አቃቤ ህጎችን ዛሬ አስመርቋል። የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቢሮ ሃላፊ አቶ ጉዮ ዋሪዮ እንደገለፁት፤ ኢንስቲትዩቱ የፍትህ ሪፎርሙን ለማሳካት የሚደረገውን ጥረት በጥናትና ምርምር እንዲሁም የህግ ሙያተኞችን አቅም በማጎልበት እያገዘ ይገኛል።   በክልሉ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በሙያና በስነ ምግባር የበቃ የሰው ሃይል ለማፍራት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አክለዋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ አህመድ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ የክልሉን የህግ ባለሙያዎች በዕውቀትና ክህሎት በማብቃት ረገድ አበረታች ስራዎች እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።   በክልሉ የፍትህ ሪፎርም ለመተግበር ሙያተኞችን በማሰልጠንና በጥናትና ምርምር እየደገፈ መሆኑን ጠቁመዋል። ቀልጣፋና ፈጣን የፍትህ አገልግሎት በመስጠት ማህበረሰቡን በታማኝነት ማገልገል ይገባል ያሉት ዳይሬክተሯ ለዚህም በስነ ምግባር የታነጸ ባለሙያ ማፍራቱን ጠቅሰዋል።   ከተመራቂዎች መካከል አቶ ጎሎልቻ ሹንዴ እንደገለፁት በቆይታቸው የህግ እውቀትን ከስነ ምግባር ጋር የሚያጣምሩበትን ዕውቀት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። በክልሉ ፈጣን የፍትህ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተሰጣቸውን ሃላፊነት በአግባቡ እንደሚወጡ አመላክተዋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት እያገዘ ነው
Jun 28, 2026 202
ደሴ/ገንዳ ውኃ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ወሎ እና በምዕራብ ጎንደር ዞኖች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት እያገዘ መሆኑ ተገለጸ። በዞኖቹ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሃሳብ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።   በደቡብ ወሎ ዞን በተካሄደ ንቅናቄ መድረክ ላይ የተገኙት የዞኑ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ቤተልሔም ብርሃኑ እንደገለጹት፣ በዞኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አረጋግጧል።   ተግባሩን ለማስቀጠልም በክረምት ወራት ከ1 ሚሊዮን በላይ በጎ ፈቃደኞችን በማሳተፍ ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የአቅመ ደካሞችን ቤት የመገንባትና የመጠገን፣ ደም የማሰባሰብ እንዲሁም የአቅመ ደካማ አርሶ አደሮችን መሬት የማልማት ሥራ ይከናወናል ብለዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአብሮነት ባህልን እያጎለበተ ነው ያሉት ደግሞ በተንታ ወረዳ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና የወጣቶች ንቅናቄና ተሳትፎ ቡድን መሪ ወይዘሮ ባንችአለም በየነ ናቸው።   በተያያዘ ዜና የምዕራብ ጎንደር ዞን ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትዕግሥት እማኘው እንደገለጹት በዞኑ በክረምቱ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ237 ሺህ በላይ ዜጎች ይሳተፋሉ። ወጣቶች፣ ባለሃብቶች እና ህብረተሰቡን በሚያሳትፈው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የልማት ሥራዎችን በማከናወን ከ280 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።   በአገልግሎቱም 612 መኖሪያ ቤቶችን መስራት፣ ከ5 ሺህ ሄክታር በላይ የአቅመ ደካሞችን መሬት ማልማት፣ የአረንጓዴ ልማት እንዲሁም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግና ሌሎች በጎ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ እንዳሉት፣ በዞኑ በበጋው ወራት የተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች የበርካታ ወገኖችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች አቃለዋል።   ህዝቡ በበጋ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያከናወነውን መልካም ተግባር በክረምቱ ወቅትም በስፋት ማስቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። በዞኖቹ በተከሄደ የንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ ላይ በጎ ፈቃደኞች፣ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢኮኖሚ
በደቡብ ወሎ ዞን በተያዘው የመኸር እርሻ ከ224 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ይለማል
Jun 28, 2026 266
ደሴ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ወሎ ዞን በምግብ ራስን ለመቻልና የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦትን ለማሳደግ በመኸር እርሻ ከ224 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዞኑ ለስንዴ ሰብል ልማት ምቹ በመሆኑ በተያዘው የመኸር እርሻ ስንዴን በስፋት ለማልማት ዝግጅት ተደርጓል። በዚህም በክረምቱ ከ224 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ በማልማት ከ9 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል ብለዋል።   የስንዴ ልማት ምርታማነትን ለማሳደግም ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ሰው ሰራሽ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑንም ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለስንዴ ልማት የተሰጠው ትኩረት አርሶ አደሩን ውጤታማ ከማድረግ ባለፈ በምግብ ራሱን ለመቻልና ለኢንዱስትሪ የሚሆን ግብአት እንዲያቀርብ ማስቻሉንም ተናግረዋል። ስንዴን በሜካናይዜሽን፣ በኩታ ገጠም እና በአዳዲስ አሰራሮች ታግዞ ማምረት መቻሉ እየተገኘ ላለው ውጤት መሰረት መሆኑንም አመልክተዋል። በዞኑ ጀማ ወረዳ የቀበሌ 08 ነዋሪ አርሶ አደር እንድሪስ አበበ በሰጡት አስተያየት እንዳሉት፣ ሁለት ሄክታር መሬታቸውን በስንዴ ለማልማት ማሳቸውን ደጋግመው በማረስ ለዘር ሥራ አዘጋጅተዋል። በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ ታግዘው በማልማትና የሰብል እንክብካቤ ሥራ በማከናወን እስከ 90 ኩንታል ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውንም ገልጸዋል። በዘንድሮው የመኸር ወቅት አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸው ላይ ስንዴ ለማልማት እንደተዘጋጁ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በወረኢሉ ወረዳ የቀበሌ 04 ነዋሪ አርሶ አደር አህመድ ታደሰ ናቸው። ቀደም ሲል ለስንዴ ልማት ብዙም ትኩረት እንደማይሰጡ አስታውሰው፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ስንዴን ማልማት ባህል በማድረጋቸው ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት በመኸር ወቅት በስንዴ ከለማው 200 ሺህ ሄክታር መሬት ከ6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ለማወቅ ተችሏል።
በኦሮሚያ ክልል ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል
Jun 28, 2026 354
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ የልማትና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ሰፊ የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። በኦሮሚያ ክልል ከ3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገብ የቻሉ 1 ሺህ 195 የሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ወደ ላቀ የኢንቨስትመንት ደረጃ የማሸጋገር ፕሮግራም በአዳማ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የጨፌ ኦሮሚያ የከተማ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አብዱልቃድር ሁሴን እንደገለጹት፤ ኢንተርፕራይዞቹ ከመንግሥት የተሰጣቸውን ዘርፈ-ብዙ ድጋፎችና ምቹ ፓኬጆችን በአግባቡ ወደ ተግባር በመቀየር ለዚህ ስኬትና የሽግግር ደረጃ በቅተዋል።   የክልሉ መንግሥት ድህነትን ለመቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም የስራ አጥነት ችግርን በዘላቂነት ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል። ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች ባስመዘገቧቸው ስኬቶች ሳይዘናጉ፣ ይበልጥ ለላቀ ውጤት ለመብቃት በሚሰማሩበት የኢንቨስትመንት መስክ ላይ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸውም አቶ አብዱልቃድር አስገንዝበዋል። የኦሮሚያ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ኤባ ገርባ በበኩላቸው፤ ኢንተርፕራይዞቹ በተሰማሩባቸው የሥራ መስኮች ውጤታማ በመሆን ወደ ኢንቨስትመንት ደረጃ መሻገራቸውን ገልጸዋል።   በተጨማሪም በመጠናቀቅ ላይ ባለው የበጀት ዓመት ብቻ ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አዲስ የሥራ ዕድል ማመቻቸት መቻሉን ኃላፊው ይፋ አድርገዋል። ኃላፊው አክለውም፤ ወደ ሥራ ለገቡ ዜጎች ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦት መሰራጨቱንና ከ10 ሺህ በላይ የሊዝ ማሽነሪዎችም ለኢንተርፕራይዞቹ መሰጠታቸውን ጠቅሰዋል።   ለሥራ አጥ ዜጎች ከተፈጠሩት የሥራ ዕድሎች መካከል የጎጆ ኢንዱስትሪ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ንግድ፣ ግብርና፣ አገልግሎት፣ ግንባታ እንዲሁም የብረታ ብረትና የእንጨት ሥራ በዋናነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተመሳሳይ በበጀት ዓመቱ ከ200 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የክልሉ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ማመቻቸት መቻሉን ገልጸዋል። ወደ ሥራ ለገቡ ዜጎች የመሥሪያና መሸጫ ቦታዎች እንዲሁም ማዕከላት መተላለፋቸውን የገለጹት ኢንጂነር ኤባ፤ በዚህም ድህነትን በመቀነስ ረገድ ወሳኝ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።   የአዳማ ከተማ ምክትል ከንቲባ ማቲያስ ሰቦቃ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በከተማዋ ሥራ አጥነትን ለመቀነስና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ። በአዳማ በጎጆ ኢንዱስትሪ፣ በከተማ ግብርና በተለይም በዶሮ እርባታ፣ በወተት ላሞች ማድለብና በሰብል ልማት ዘርፎች ለሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ጂኦ-ስትራቴጂክ ተጠቃሚነት ለማስጠበቅ የድንበርና የኤርፖርት ደኅንነቶችን ማዘመን ወሳኝ ጉዳይ ነው 
Jun 28, 2026 423
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያን ጂኦ-ስትራቴጂክ ተጠቃሚነት ለማስጠበቅ የድንበርና የኤርፖርት ደኅንነቶችን ማዘመን ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራልና የኤርፖርትና ድንበር አስተዳደር ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራም ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ። የተቀናጀ የኤርፖርት እና የድንበር አስተዳደር ትራንፎርሜሽን ፕሮግራም ላይ ያተኮረ የምክክርና የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራልና የኤርፖርትና ድንበር አስተዳደር ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራም ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በዚሁ ወቅት፤ የትራንስፎርሜሽን ፕሮግራሙ የኢትዮጵያን የደኅንነት ስጋቶች አስቀድሞ ለመከላከል፣ የሳይበር ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና በዲጂታል ዘመን ኢትዮጵያ ያላትን ተወዳዳሪነት ለማስቀጠል ወሳኝ ነው ብለዋል። ፕሮግራሙም ስጋቶችን በመረጃ አስደግፎ ለማወቅና ለመከላከል እንዲሁም በተቋማት መካከል የመረጃ ልውውጥን በማሳደግ ሽብርተኝነት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች፣ የገንዘብና የመሣሪያ ዝውውርን በጋራ ለመመከት አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ፕሮግራሙ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች እንዲለሙ በማድረግ የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥና አሰራሮች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲደገፉ ግብ የጣለ መሆኑንም አስረድተዋል። ለዚህም ስኬት የተዘጋጀው ፍኖተ-ካርታ የሚያስፈልጉትን የቴክኖሎጂ አቅም፣ የአሠራር ሥርዓቶች ስታንዳርድ፣ የሰው ሀብት፣ የመሠረተ-ልማት አቅርቦት እንዲሁም የሕግና የቁጥጥር ጉዳዮችን ለይቶ ማስቀመጡንም አብራርተዋል።   ፕሮግራሙ የሀገሪቱን የጂኦ-ስትራቴጂክ ቁመና ለማስጠበቅና የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አንዱ ማስፈጸሚያ መሣሪያ እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ጂኦ-ስትራቴጂክ ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የድንበርና የኤርፖርት ደኅንነቶችን ማዘመን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በዚህም ሀገሪቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ፍኖተ-ካርታው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ግቦችን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፣ ሀገሪቱ በቀጣይ ለምታስተናግደው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል። በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የጸጥታ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።
የቦንጋ ከተማን እድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 
Jun 28, 2026 299
ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስተዳደር አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ለቀጣይ አሥር ዓመታት ተግባራዊ የሚያደርገው የቦንጋ ከተማ ስትራክቸራል ማስተር ፕላን ላይ ያተኮረ የሕዝብ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።   ይህ አዲስ ስትራክቸራል ፕላን የከተማዋን የመሠረተ ልማት አቅርቦት፣ የመኖሪያ ቤት ፍላጎት፣ የአረንጓዴ ስፍራዎችን አጠባበቅ እና የኢንዱስትሪ ቀጠናዎችን በዘመናዊ መንገድ ለመምራት የተነደፈ መሆኑም ተገልጿል። ዕቅዱ በቀጣይ አሥር ዓመታት ከተማዋን በፕላን በመምራት በዘፈቀደ የሚደረጉ ግንባታዎችን ለመግታትና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ለመዘርጋት ትልቅ መሠረት ይጥላል ተብሎም ይጠበቃል። በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ፤ የቦንጋ ከተማ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረች እድሜ ጠገብ ከተማ መሆኗን ተናግረዋል። ከተማዋ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ ሳታድግ መቆየቷን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው፤ አሁን ላይ መንግሥት ለከተሞች ዕድገት ከሰጠው ልዩ ትኩረት በመነሳት፣ የቦንጋን ዕድገት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። የከተማዋን ፕላን በአዲስ መልክ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ ከኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ጋር ውል በመግባት ሰፊ ጥናትና ምርምር ሲደረግ መቆየቱን ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል። ፕላኑ ላይ ከዚህ ቀደም የተለያዩ የውይይት መድረኮች ሲደረጉ መቆየታቸውን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው፤ በዛሬው የሕዝብ መድረክ ላይ የሚሳተፉ የኅብረተሰብ ክፍሎችም አስፈላጊውን ሐሳብና አስተያየት በመስጠት ለከተማዋ ዕድገትና ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። ቦንጋ ከተማ ደረጃዋን የጠበቀችና ለነዋሪዎቿ ምቹ እንድትሆን በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተክለአብ ቡሎ(ዶ/ር) የገለጹ ሲሆን፤ አዲሱ ማስተር ፕላንም ለዚህ ስኬት ትልቅ ድርሻ እንደሚኖረው አስታውቀዋል።   አዲሱ ስትራክቸራል ፕላን የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር መሠረት ያደረገ መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባው፤ ከተማዋን ለልማት፣ ለመኖሪያ ቤት፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ ከማድረግ ባለፈ የገቢ አቅሟን የሚያሳድግ መሆኑንም ጠቁመዋል። ከዚህም ባሻገር ፕላኑ ለሕብረተሰቡን የረጅም ጊዜ የመልማት ፍላጎት ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን ከንቲባው ገልጸው፤ አሁን እየተካሄደ ያለው ውይይት አስፈላጊ ግብዓቶችን በማካተት ፕላኑ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ለሚቀጥሉት አሥር ዓመታት የሚያገለግለው ይህ አዲስ ፕላን፤ የከተማዋን ነባር 6 ሺህ 300 ሄክታር ስፋት ወደ 15 ሺህ ሄክታር በላይ ያሳደገ መሆኑ በውይይቱ ላይ ተመልክቷል። በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የዩኒቨርሲቲው የኢንኩቤሽን ማዕከል የፈጠራና ክህሎት ውጤቶችን የምናስተዋውቅበት ምቹ ምኅዳር ፈጥሮልናል 
Jun 28, 2026 251
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የኢንዱስትሪ ኢንኩቤሽን ማዕከል የቴክኖሎጂ ፈጠራና ክህሎት ውጤቶችን ለኢንዱስትሪዎች የሚያስተዋውቁበት ምቹ ምኅዳር እንደፈጠረላቸው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሙያተኞች ገለጹ። የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የፈጠራ ሙያተኞችን ከኢንዱስትሪዎችና አጋሮች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ የፈጠራ ሥራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ማስተዋወቂያ መድረክ ማካሄዱ ይታወቃል።   በመድረኩም በዩኒቨርሲቲው የኢንዱስትሪያል ኢንኩቤሽን ማዕከል በተማሪዎችና በተመራማሪዎች የተሰሩ የፈጠራና ክህሎት ውጤቶች ቀርበዋል። የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ከማል ኢብራሂም (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢንኩቤሽን ማዕከሉ ለተማሪዎችና የፈጠራ ሙያተኞች ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።   የማዕከሉ ዋና ዓላማ ተማሪዎች የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ፈጣሪና ኢንተርፕርነር የሚሆኑበትን ዓለም አቀፍ መደላድል መፍጠር መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም የዩኒቨርሲቲው የኢንዱስትሪ ኢንኩቤሽን ማዕከል ተማሪዎችን፣ ተመራማሪዎችንና ኢንዱስትሪዎች በአንድ ቦታ የሚገናኙበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንዳስቻለ አስረድተዋል። የስሪ ዲ ፕሪንቲንግ ዲጂታል ኮንስትራክሽን የቤት መሥሪያ ማሽን ያለሙት ዮሐንስ ረጋሳ (ዶ/ር)፤ ማዕከሉ የፈጠራ ባለቤቶችንና የኢንዱስትሪ አጋሮች በቀጥታ የሚገናኙበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።   ለዕይታ ያቀረቡት የስሪ ዲ ዲጂታል ኮንስትራክሽን ማሽንም በኮምፒውተር የታገዘ ዲዛይንን ወደ ማሽን ቋንቋ በመቀየር በውስን የሰው ሃይል ጊዜ ቆጣቢና ጥራት ያለው ግንባታን ማከናወን እንደሚያስችል ገልጸዋል። የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ የፈጠራ አቅምን መጎልበት የአሰራር ሥርዓቶችን በራስ አቅም በማሳለጥ ዘመናዊ ተግባራትን ለማከናወን ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል። ሌላኛው የፈጠራ ባለቤት ወጣት ሳሙኤል አለሙ በበኩሉ፤ በሀገር በቀል የምህንድስና ዕውቀት የለስላሳ መጠጦችን መሸጥና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ተንቀሳቃሽ የቬንዲንግ ማሽን ማልማቱን ገልጿል። የቬንዲንግ ማሽኑም የሁሉንም ባንኮች የክፍያ አማራጭና የደንበኞችን ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ በማንኛውም ሰዓት ያለአንዳች ኃይል መቆራረጥ ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ተናግሯል። ቬንዲንግ ማሽኑ ለትምህርትና ጤና ተቋማት ጭምር ተመራጭና ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጥ ነው ብሏል። ተማሪዎችም በትምህርት ቤት ቆይታቸው የሚያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት በማጎልበት ለሚስተዋሉ የቴክኖሎጂ ክፍተቶች መፍትሔ መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝቧል።
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 28, 2026 207
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። በኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ የፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚዎች ቁጥር ወደ 90 ሚሊየን ለማድረስ ግብ መቀመጡ ይታወቃል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በታህሳስ ወር ”ፋይዳ ለሴቶች” ሀገር አቀፍ የንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብርን አስጀምሯል። ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ከይረዲን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሴቶችን የዲጂታል አገልግሎቶች ተጠቃሚነት ለማላቅ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤትነትና ተደራሽነት በስፋት እየተሰራበት ይገኛል።   ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራምና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበርም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሴቶች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በእስካሁኑ ሂደት 26 ሚሊየን ሴቶችን የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ባለቤት በማድረግ የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተደራሽነትም የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል የሴቶችና ሕፃናት ምክትል ቢሮ ኃላፊ ሰሚራ ፋሪስ፤ በከተማና ገጠር የሚኖሩ የክልሉ ሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።   የሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤትነትም ሁለንተናዊ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። በአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዝና ጌታቸው በበኩላቸው፤ የሴቶችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤትነት ለማረጋገጥ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጭምር እየተሰራበት ነው ብለዋል።   በዚህም ከባድርሻ ተቋማት ጋር በመተባበር በተከናወነ ሥራ በ2018 ዓ.ም እስካሁን ድረስ ከ5 ሚሊየን በላይ የክልሉ ሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ማድረግ መቻሉን አስታውቀዋል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሴቶችና ሕፃናት ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊና የሴቶች ዘርፍ ኃላፊ ነጅሚያ ራህመቶ በበኩላቸው፤ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።   በዚህም የአደረጃጀቶችን ንቅናቄ በመጠቀም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሴቶችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ማድረግ እንደተቻለ አስረድተዋል። በጋምቤላ ክልል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አረየት ዑጁሉ በበኩላቸው፤ በክልሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ በማካሄድ ሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።   ይህም በተለያዩ አገልግሎቶች ላይ የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የልማት አካል እንዲሆኑ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ለኢትዮጵያ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ስኬት የበኩላችንን እንወጣለን - ተመራቂ ተማሪዎች
Jun 27, 2026 1097
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ለኢትዮጵያ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ስኬት በተማሩበት የሙያ መስክ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ ምረቃ፣ በድህረ ምረቃ እና በሦስተኛ ዲግሪ በመደበኛና በተከታታይ የትምህርት ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 246 ተማሪዎች አስመርቋል።   የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተርና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ ትዕግሥት ሀሚድ፤ ተመራቂዎች የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞ ለማፋጠን ዕውቀታቸውን ወደ ፈጠራ ማሸጋገር አለባቸው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞ ዳር ለማድረስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ባለሙያዎችን ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል።   ሀገሪቱ አሁን ካለችበት የኢኮኖሚና የቴክኖሎጂ ደረጃ ከፍ እንድትል የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተመራቂዎች ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ፈጠራና ኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅም እንዲለውጡ በማስገንዘብ ሀገራቸውን በቅንነት እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ሰፊ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል።   ትምህርት ግቡን እንዲመታ ከተደራሽነቱ ባሻገር ጥራቱን ማረጋገጥ የግድ መሆኑን ጠቅሰው፥ መንግሥት ከቅርብ ዓመታት ውዲህ ብቁ ትውልድ ለማፍራት የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ሪፎርም አድርጎ ወደ ሥራ መግባቱን አብራርተዋል። በዚህም ሳይንስና ቴክኖሎጂን ጨምሮ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ነው የገለጹት። የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ደረጄ እንግዳ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ሲያስመርቅ የዘንድሮው ለ12ኛ ጊዜ መሆኑን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያን የልማት ግቦች ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።   ተመራቂ ተማሪዎች በተግባር ተኮር የቴክኖሎጂ ፈጠራና በኢንዱስትሪዎች ውስጥ በሚታዩ ተጨባጭ ችግሮች ላይ ያተኮሩ ችግር ፈቺ የምርምር ሥራዎችን ማከናወናቸውን አመላክተዋል። ዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማሳለጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን በእጅጉ እያሳደገ እንደሚገኝ አንስተዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመራቂ ተማሪዎች እንደ ሀገር የተጀመረው የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ግቡን እንዲመታ በተማሩበት የቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ተመራቂ፣ የማዕረግ ተሸላሚና የዋንጫ አሸናፊ አፎምያ ቱጋሳ፤ ለዚህ ስኬት የበቃሁት ሁሌም ለትምህርቴ ቅድሚያ ሰጥቼ መማርና ማጥናት በመቻሌ ነው ብላለች፡፡ ወደፊትም በሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ በማሽን ለርኒንግ እና በተያያዥ የቴክኖሎጂ መስኮች በመሰማራት ለሀገሯ የበኩሏን አስተዋፅኦ ለማበርከት መዘጋጀቷን ገልጻለች፡፡   ሌላኛዋ የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ተመራቂና የማዕረግ ተመራቂ አርሴማ ተስፋዬ በበኩሏ፣ በተማረችበት የቴክኖሎጂ ዘርፍ ሀገሯን ለማገልገል ዝግጁ መሆኗን ተናግራለች፡፡ በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ የተመረቀችው ሰሚራ አለዉ፣ ቴክኖሎጂ ለሀገር ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሳ፣ በተማረችበት የትምህርት መስክ ለሀገሯ የበኩሏን አስተዋፅኦ እንደምታበረክት ገልጻለች።   በአምስት ዓመት ቆይታው የህይወት ልምድና እውቀት የቀሰመ መሆኑን ጠቅሶ፤ በተማረበት ሙያ ሀገሩን ለማገልገል እንደሚሰራ የገለጸው ደግሞ የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ተመራቂ ታዴዎስ ደጀኔ ነው፡፡   በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።  
ዩኒቨርስቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ እና በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ላይ በትኩረት እየሰራ ነው
Jun 27, 2026 568
አሶሳ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ አሶሳ ዩኒቨርስቲ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች በክህሎት የታነፀ ትውልድ ለማፍራት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። ዩኒቨርስቲው በ13ኛ ዙር በመደበኛ፣ በተከታታይ እና በክረምት መርሃግብር ያስተማራቸውን 673 ተማሪዎች አስመርቋል።   የአሶሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ያሬድ ሙሉ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርስቲው በተግባር ተኮር ሳይንስ ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የምርምር ስራዎችን በማከናወን አበረታች ውጤት እያስመዘገበ ነው። በተለይም በግብርና፣ እና በማዕድን ዘርፍ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን በማውጣት የአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንዲሆን እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ዩኒቨርስቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታነፀ እና በክህሎት የበለፀገ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረገው ሂደት የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልፀዋል። በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በበኩላቸው፤ ተመራቂዎች ሀገሪቱ ለምትፈልገው የተማረ የሰው ሀይል ተጨማሪ አቅም ይሆናሉ ብለዋል።   ተመራቂዎች ለኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የብልጽግና ጉዞ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸውም ነው ያሳሰቡት። በመርሃ ግብሩ ላይ በባህልና ስፖርት ሚኒስትር የባህልና ቋንቋ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሀዲ፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ስፖርት
ሸገር ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ መቆየቱን አረጋገጠ
Jun 28, 2026 275
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሸገር ከተማ መቻልን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍቅሩ አለማየሁ እና ያሬድ መኮንን ግቦቹን አስቆጥረዋል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን ያስመዘገበው ሸገር ከተማ በ47 ነጥብ ከነበረበት 15ኛ ደረጃ ወደ 10ኛ ከፍ ብሏል። ዘንድሮ ከከፍተኛ ሊግ ያደገው ሸገር ከተማ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል። በሊጉ ዘጠነኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቻል በ56 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሃዋሳ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሀሰን ሁሴን በ34ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪ ሆኗል። ጌታነህ ከበደ በ61ኛው ደቂቃ የሃዋሳ ከተማን የአቻነት ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ51 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ሃዋሳ ከተማ በ50 ነጥብ ስምንት ደረጃ ላይ ይገኛል። ዛሬ አስቀድመው በተደረጉ የ37ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና ባህር ዳር ከተማን 1 ለ 0፣ ወላይታ ድቻ አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፈዋል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 37ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የፕሪሚየር ሊጉ የመጨረሻ ሳምንት (38ኛ ሳምንት) መርሐ ግብር በቀጣይ ሳምንት ይካሄዳል።
የ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ደቡብ አፍሪካ እና ካናዳ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀመራል
Jun 28, 2026 386
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ ያደረገው የ32 ዙር (Round of 32) የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል። የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብሩ ደቡብ አፍሪካ እና ካናዳ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀመራል። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ በሎስ አንጀለስ ስታዲየም ይካሄዳል። ደቡብ አፍሪካ በምድብ አንድ በአራት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በተለይም በምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ኮሪያ ሪፐብሊክን ማሸነፏ ወደ ጥሎ ማለፍ እንድትገባ አስችሏታል። ተጋጣሚዋ ካናዳ በምድብ ሁለት በአራት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ መጨረሷ ይታወቃል። ከዓለም ዋንጫ አስተናጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ካናዳ በምድቧ ኳታርን 6 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ያሸነፈችበት ጨዋታ በውድድሩ ታሪክ ያስመዘገበችው የመጀመሪያ ድሏ ሆኗል። ደቡብ አፍሪካ እና ካናዳ ወደ ጥሎ ማለፍ ሲገቡ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። በዓለም ዋንጫው እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። ከዚህ ቀደም የነበራቸው ብቸኛ ግንኙነት እ.አ.አ በ2007 በደርባን ያደረጉት የወዳጅነት ጨዋታ ነው። በወቅቱ ደቡብ አፍሪካ ቴኮ ሞዲሴ በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠራቸው ጎሎች 2 ለ 0 ማሸነፏ የሚታወስ ነው። ሁለቱ ሀገራት ከእግር ኳስ ውጪ በዓለም መድረክ በራግቢ እና ክሪኬት ስፖርቶች ተቀናቃኝነት ያላቸው ሀገራት ናቸው። ሀገራቱ ወደ ቀጣዩ የጥሎ ማለፍ ምዕራፍ ለመሸጋገር የሚያደርጉት ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል። አሸናፊው ሀገር ወደ 16 ውስጥ መግባቱን ያረጋግጣል። የ32 ዙር (Round of 32) የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር እስከ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ 48 ሀገራት እየተሳተፉ ይገኛል። የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ወደ 48 በማደጉ ምክንያት የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) የ32 ዙር (Round of 32) የጥሎ ማለፍ ፎርማት በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ አድርጓል። በምድብ ጨዋታዎች ወቅት 48ቱ አገራት በ12 ምድቦች (ከምድብ 1 እስከ 12) ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። በ12ቱ ምድቦች አንደኛ እና ሁለተኛ የወጡ 24 ሀገራት እንዲሁም ከየምድባቸው በሶስተኛነት ካጠናቀቁት 12 ብሔራዊ ቡድኖች መካከል ስምንቱ በምርጥ ሶስተኛነት ወደ ጥሎ ማለፍ ዙሩ ገብተዋል።
አካባቢ ጥበቃ
አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ አዲስ ድንቅ ስጦታ አበርክታለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 28, 2026 300
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ አዲስ ድንቅ ስጦታ አበርክታለች ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ አዲስ አበባችን የነዋሪዎቿን ጥያቄዎችና መሠረታዊ ፍላጎቶች በተጨባጭ እየመለሰች፣ ለሕዝባችን ቅድሚያ የሚሰጣቸውንና ከተማዋ የሚመጥናትን ታላላቅ የልማት ሥራዎች ሁሉ በላቀ ብቃትና ትጋት እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል። ዛሬ ለከተማችን አዲስ አበባ ድምቀትና ተጨማሪ ጌጥ እና የውበት ፀዳል ያላበሰውን ይህን የወንዝ ዳርቻ እና የግድብ ልማት በጠቅላይ ሚኒስትራችን ሐሳብ አመንጪነት በተሰጠን የሥራ መመሪያ መሠረት በጥራትና በፍጥነት አጠናቀን ለሕዝብ አቅርበናል ሲሉም ገልጸዋል።   ፕሮጀክቱ በከተማዋ ከተሰሩት ሌሎች የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች ጋር ተዋህዶ ሲታይ በእርግጥም አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርጧ የቱሪስት መዳረሻ ብቻ ሳትሆን የውበት ማማ የሚያደርጋት ድንቅ ፕሮጀክት መሆኑን ከንቲባዋ ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 87.6 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሲሆን፣ 10.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው፤ በውስጡም እጅግ ማራኪ የሆኑ የጋራ አገልግሎት መስጫዎችንና የሕዝብ መገልገያዎችን አሟልቶ ይገኛል ብለዋል፡፡ ይህም 1 ትልቅ ግድብ፣ 16 አነስተኛ ግድቦች፣ 3 ቼክ ዳሞች፣ 1.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሐይኪንግ፣ እንዲሁም 20.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ ድጋፍ ግድግዳን (Retaining Wall) ማካተቱን አንስተዋል።   የተፈጥሮ ውበቱን ይበልጥ ለማጉላትም 3 ማራኪ ፏፏቴዎች እና 1 የውሃ ምንጭ ግንባታ የተከናወነ ሲሆን፣ የመሬት ጥበቃን ለማረጋገጥ 36,928 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው የኮንሶ ጋቢዮንና የኮንሶ እርከን ሥራዎች ተሠርተውለታል ብለዋል፡፡ ልማቱ ለተፈጥሮ በሰጠው ልዩ ትኩረት፣ 59.7 ሄክታር የሚሸፍን ውብ የአረንጓዴ ልማት ስፍራን ያበለፀገ ሲሆን፣ 50,330 የተለያየ ዝርያ ያላቸው ዛፎችም እንደተተከሉበት ገልጸዋል። ከመሠረተ-ልማት አቅርቦት አኳያ 10.62 ኪሎ ሜትር ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ፣ 33.2 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገዶች፣ እና 33.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ዘመናዊ የመንገድ መብራት ዝርጋታ መከናወኑን አንስተዋል።   በተጨማሪም 19.13 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ እና የጎርፍ ማስወገጃ መስመር፣ እንዲሁም 23 ንፁህ የመጸዳጃ ቤቶች ተገንብተዋል። ጎብኚዎች ወንዙን በቀላሉና በውበት እንዲሻገሩ ለማስቻል 21 የእግረኛ ድልድዮች፣ 3 ተንጠልጣይ ድልድዮች፣ 6 የእግረኛ የብረት ድልድዮች፣ 1 ሰርኩላር ድልድይ እና 1 የኮንክሪት ድልድይ ተሠርተዋል። ማኅበረሰቡ ዘና እንዲልና የተሟላ አገልግሎት እንዲያገኝ በማሰብም፤ 9 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ በአንድ ጊዜ 695 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ 7 የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች (ፓርኪንጎች)፣ 4 የመሰብሰቢያ ስፍራዎች፣ 7 ፕላዛዎች እና 4 ፓቪሊዮኖች ተገንብተዋል። ለንግድና ለመዝናኛ አገልግሎት የሚውሉ 32 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ሱቆች፣ 2 አንፊ ቲያትሮች (Amphitheaters)፣ 10 ካፌቴሪያዎች፣ 7 የልጆች መጫወቻ ስፍራዎች፣ እንዲሁም 2 አነስተኛ የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት ተካተውበታል።   ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በታለመለት የጊዜ እና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ ሌሊት ከቀን የደከማችሁና የታተራችሁ፣ ያስተባበራችሁና የደገፋችሁ በየደረጃው የምትገኙ አመራሮች፣ እንዲሁም ለመላው የአካባቢው ማኅበረሰብ በከተማ አስተዳደሩ እና በራሴ ስም ላቅ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)  የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን መረቁ
Jun 28, 2026 210
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ይህ ሰፊ መሰረተ ልማት የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎችን በጋራ የያዘ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለት የተመረቀው ፕሮጀክት 87 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት የሚሸፍን መሆኑን የገለጹ ሲሆን 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት እንዳለው አመልክተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ የግንባታ ስኬት ብቻ ሳይሆን መዲናዋን የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋምና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች፣ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ የጀመርነውን ስልታዊ ሽግግር የሚያፋጥን ታላቅ አጋጣሚ ነው ብለዋል። ‎ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ህልሞቻችን እስከሚሳኩ በብርታት እንሠራለን - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 28, 2026 537
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ)፡- በሁሉም መስክ አቅደን የምንተገብራቸው ህልሞቻችን እስከሚሳኩ ድረስ በብርታት እንሠራለን ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ አረንጓዴ ዐሻራ ከእሳቤ እስከ ትግበራው ኢትዮጵያ የተገለጠችበት ደማቅ ብሔራዊ ቀለም ነው ብለዋል። በእሳቤዎች የተመሩ የታላላቅ ስልጣኔዎች እና የነጠሩ እውቀቶች ማሕደር በሆነችው ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ እሳቤ ይህ ትውልድ የአርቆ አሳቢ አባቶቹ ልጅ መሆኑን ያስመሰከረበት የጠራ ሐቅ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። የአየር ንብረት ለውጥ በተለምዶ ከምናየው ተደጋጋሚ የኮንፈረንስ እቅድ በተሻገረ፤ አፈር ነክቶ ጭቃ ረግጦ በትጋት በመስራት የሚመጣ የትጋት ውጤት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ ከማመንጨት እስከ ትግበራ በመምራትና በመሥራት ግንባር ቀደም ሆነው አሳይተውናልም ብለዋል። የጠራ እቅድ እና መዳረሻ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ ሀገራዊ ፕሮጀክት ከታዳጊ ህጻናት ጀምሮ የእድሜ በረከት እስከበዛላቸው አረጋውያን የተሳተፉበት ታሪካዊ የልማት ዘመቻ ሆኗል ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። የኢትዮጵያ ልጆች ለዓመታት በስኬት የተገበሩት ይህ ኢኒሼቲቭ ሀገራችንን በዓለም ፊት በክብር እያስጠራ ያለ የለውጥ ምልክት እስከመሆን ደርሷል ሲሉም አስታውቀዋል። እንደ ኮፕ 32 ያሉ ዓለም አቀፍ መድረኮችን የማስተናገድ እድሎችም በተባበረ ክንድ በተደመረ እሳቤ የመስራታችን ውጤቶች እና የብሔራዊ ዐሻራችን ሽልማቶች ናቸው ብለዋል። በአረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች የለውጥ ግቦቻችን የታዩ የትጋት ድል ፍሬዎች በተደመሩ ጥረቶች ኢትዮጵያ በእርግጥም እየለማች እየፈካች ትገኛለች ብለዋል። በሁሉም መስክ አቅደን የምንተገብራቸው ህልሞቻችን እስከሚሳኩ ድረስ በብርታት እንሠራለን ሲሉም ገልጸዋል በመልዕክታቸው። ‘ተስፋን እንትከል’ ሲሉም ሕብረተሰቡ በችግኝ ተከላ በንቃት እንዲሳተፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በክልሉ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተከናወኑ ተግባራት ምርታማነት እንዲጨምር አስችለዋል
Jun 27, 2026 652
ጎጀብ፤ ሰኔ 20 /2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተከናወኑ ተግባራት ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻላቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ክልላዊ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላን ''ተስፋን እንትከል'' በሚል መሪ ሐሳብ በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ጎጀብ ቀበሌ በመገኘት በይፋ አስጀምረዋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት፤ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የተተከሉ ችግኞች የአፈር መሸርሸርን በመከላከል፣ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ እንዲጨምር አድርገዋል። እንዲሁም የከርሰ ምድርና ገፀ ምድር የውሃ ሀብት ክምችት በመጨመሩ ምርታማነት እንዲያድግ አስችለዋል ብለዋል። በዘንድሮው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከበፊቱ በተለየ መልኩ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሻይ ቅጠል ችግኞች የሚተከሉ መሆኑን ጠቁመው ይህም ለክልሉ ተደማሪ አቅምን እንደሚፈጥር አመልክተዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ኢያሱ ኤልያስ በበኩላቸው በቀደሙት ጊዜያት በነበረዉ የተዛባ እይታ የተፈጥሮ ሀብቶቻችንን በተገቢና በዘላቂነት መጠቀም አልቻልንም ብለዋል።   በዚህም ሳቢያ ሀገራችን በምግብ ራሷን መቻል አቅቷት ተመፅዋች ሆና መቆየቷን ገልጸው ይህን ታሪክ በመቀየር ኢትዮጵያ ያላትን የውሃ፣ የመሬትና ሌሎች ሀብቶቿን በዘላቂነት ለመጠቀም ባለመ በተቀረፀው የአረንጓዴ አሻራ ኢንሼቲቭ ዘርፈ ብዙ ውጤቶች ተመዝግበዋል ነው ያሉት፡፡ በዚህም ምርታማነት ጨምሯል፤ የአፈር ለምነት አድጓል፤ የቡናና የፍራፍሬ ልማት አድጓል፤ በቤተሰብ ደረጃ የተመጣጠነ ምግብ የማግኘት ሁኔታም እያደገ መምጣቱን ነው የጠቀሱት፡፡ በክልሉ ‎የአረንጓዴ አሻራ ኢንሼቲቭ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን የገለፁት ደግሞ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ናቸው፡፡   ኢንሼቲቩ የክልሉን ስነ-ምህዳር በከፍተኛ ሁኔታ መቀየሩን ጠቁመው ጠፍተው የቆዩ አዕዋፋትና የዱር እንስሳት እንዲመለሱና የደረቁ ምንጮች እንዲጎለብቱ ማስቻሉን ገልፀው የክልሉን የደን ሽፋን ከ41 ወደ 43 በመቶ ማሳደግ ችሏል ብለዋል። ‎ ‎የ2018 ዓ.ም በክልሉ በአጠቃላይ 460 ሚሊዮን ችግኞች እንደሚተከሉ ጠቅሰው ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ የማኅበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ እንደሚተከሉም ተናግረዋል።   የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንደሻው ከበደ በበኩላቸው የአየር ንብረት ለውጥ የዜጎችን ህይወት እየፈተነ ባለበት ወቅት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ሁነኛ መፍትሔ ተደርጎ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ‎የዞኑ ማህበረሰብ ደንን ጠብቆ የማቆየት ልምዱን ከአረንጓዴ አሻራ ዕሳቤ ጋር በማጣመር የደን ሽፋኑ ላይ ከፍተኛ እመርታ እየፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመው በዞኑ በያዝነው ክረምት ወራት የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ይተከላሉ ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 13462
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 9401
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 8219
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 8116
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 565
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ከተጽዕኖ ፈጣሪነትና ተደማጭነት መጎልበት እስከ የአኅጉር ድምጽ መሆን - የኢትዮጵያን ታላቅነት የገለጠው የዲፕሎማሲው ዘርፍ ስኬት  
Jun 25, 2026 2089
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቷ የፓን አፍካኒዝም ንቅናቄን በማንሳት አኅጉራዊ ተቋማት እንዲመሠረቱ ፊታውራሪ ከመሆን ጀምሮ ለጎረቤቶቿ ሰላም ጉልኅ ሚና ተጫውታለች፤ አሁንም ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔን እያሰረጸች በርካቶች እንዲጋሯት አድርጋለች። እንደ ሀገር ከለውጡ መንግሥት ወዲህ ከተገኙ በርካታ ትላልቅ ስኬቶች መካከል በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው አንዱ ነው። ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የለውጡ መንግሥት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ዋነኛ መለኪያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ነው። የኢትዮጵያ ሁኔታዎችን የማሰብ፣ የመፈለግና የመከወን ሂደት ንጥል (ለራስ ብቻ የሚል) ሳይሆን፤ በወንድማማችነት/እህትማማችነት ዕሳቤ በጋራ ማደግን ያነገበ ነው። ይህ ሂደቷም በበርካታ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ እንዲሁም አኅጉር አቀፍ ተቋማት ተወድሷል። በዚህም ሐሳቦቿ ቅቡል ሲሆኑ ተመልክተናል። ኢትዮጵያ የ#BRICS አባል መሆን መቻሏ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ይህም ተሰሚነቷን ያረጋገጠ ማስረጃ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ተያያዥ ጉዳዮች ዘርፈ-ብዙ ጥቅም በማስገኘት የበለጸገች ኢትየጵያን ዕውን የማድረግ ጉዞው ያፋጥናል። ወዲህ ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልና አፍሪካን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና መመረጧም የአኅጉሪቱ ድምጽ መሆኗን ይነግረናል። ዓለም አቀፍ ብሎም አኅጉር አቀፍ የሆኑ በርካታ ኮንፈረንሶችም በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እንዲካሄዱ መደረጉ አንድምታው ብዙ ነው። በብቃት ማስተናገዷ ደግሞ ሌላኛው ጥንካሬዋ። ሌላው የሀገራችንን የተጨበጠ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት የሚገልጽልን፤ የዓለም የዓየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን (COP32) እንድታዘጋጅ መመረጧ ነው። ይህን ትልቅ ዕድል በርካቶች ስለተመኙት አላገኙትም፤ ኢትዮጵያ ግን ዜጎቿን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባከናወነችው ያላሰለሰ ትጋት አግኝታዋለች። ግጭት ባለባቸው የቀጣናው ሀገራትም በመንግሥታቱ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት ሥር ከምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባለፈ፤ በግሏ የሰራችው ብዙ ነው። ከራሷ አልፋ ለጎረቤቶቿ ዘብ መሆኗ፤ በአብሮነት መኖርን እና በጋራ ማደግን በተግባር የገለጠች ሀገርም ያደርጋታል። ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ በሚለው ቅድሚያ ለሀገር በቀል ዕውቀቶች በሩን ክፍት ባደረገው ትጋቷም፤ በበርካታ የአኅጉሪቱ ሀገራት ዘንድ ምሥጋና አስችሯታል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲዋም በተለያዩ ሀገራት በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎቿን ከሀገራቱ እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመነጋገር በተሳካ ሁኔታ ልጆቿን ወደ ዕቅፏ መልሳለች፤ በቅርቡ በሳዑዲ ዓረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምኅረት ዐዋጅ እንዲሰጣቸው መደረጉ አንድ ማሳያ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን ጨምሮ በተለያዩ አኅጉራት በሚገኙ ሀገራት መሪዎችና ተወካዮች ዘንድ በስፋት የተመረጠችና የተጎበኘች ሀገር መሆኗን ማስታወስ ተገቢ ነው። ከጉብኝት ባለፈ ትላልቅ ስምምነቶችም የተፈራረመች መሆኗን ልብ ማለት ይገባል፤ ይህም የምታነሳውን ሐሳብ ገዥነትና የአፍሪካ መግቢያ በር መሆኗን ያሳያል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ መሆኑን መረዳት ይገባል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድርድር ሂደት የተጎናጸፈችው የዲፕሎማሲ ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መነቃቃት መፍጠሩንም ማጤን ያስፈልጋል። ይህ የተሳካው ሀገሪቱ ኢትዮጵያ መንገዷም የጋራ ልማትን የሰነቀ ዕውነት በመሆኑ ነው። በቀጣይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለአንዲት ሀገራቸው አምባሳደር በመሆን፤ የዲፕሎማሲውን ሥራ በይበልጥ ማገዝ ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ካልሠሩ ማን ለሀገራቸው ሊሠራ ይችላል?
እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል?
Jun 25, 2026 1332
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በዝምታ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት፤ የጨጓራ፣ አንጀትና ጉበት ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሚፍታህ ደሊል ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የጉበት ጤናን እንዴት መጠበቅ እንደሚቻል፣ ለጉበት ጤና መታወክ ስለሚያጋልጡ ጉዳዮች፣ ስለጉበት ስብ (ቅባት) እንዲሁም ሕክምናው ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል። · በሰው ልጅ ሕይዎት (ሠርካዊ እንቅስቃሴ) ውስጥ የጉበት ሚና ምንድን ነው? ዶክተር ሚፍታህ እንደገለጹት፤ ጉበት በሰውነታችን ውስጥ ኪሚገኙ ትላልቅ የውስጥ አካል ክፍሎች (ኦርጋኖች) አንዱ ነው። ከ1 ሺህ በላይ ተግባራትን የሚያከናውን ትልቁ እና ባተሌ የሆነ የአካል ክፍል መሆኑንም አስረድተዋል። የኪንታሮት በሽታ መንስዔ ይታወቃል? ካንሰር እንዴት ይከሰታል? · ለጉበት ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ይታወቃሉ? ለጉበት ህመም አጋላጭ ከሆኑ መንስዔዎች መካከል፤ ቫይረሶች (ሄፓታይትስ ቢ፣ ሄፓታይትስ ሲ) እንዲሁም አልኮል (ከፍተኛ መጠን ያለው አልኮል መጠጣት) መሆናቸውን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅት ደግሞ በስፋት የሚስተዋለው አጋላጭ መንስዔ የጉበት ስብ መጨመር መሆኑንም በአጽንዖት ገልጸዋል። በእኛ ሀገር ደረጃ ከሚከሰቱ የጉበት ህመሞች 50 በመቶው በሄፓታይትስ ቢ ምክንያት የሚከሰት ነው ይላሉ ዶክተር ሚፍታህ። ከ15 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የጉበት ህመም የሚከሰተው ደግሞ በአልኮል ምክንያት መሆኑን ነው ያስረዱት። እንዲሁም በሄፓታይትስ ሲ ምክንያት የሚከሰተው የጉበት ህመም ከላይ ከተገለጹት ቀጥሎ በሦስተኛነት እንደሚቀመጥም አመላክተዋል። አሁን አሁን ደግሞ ይላሉ ዶክተር ሚፍታህ፤ በሥራም ሆነ ለመዝናናት ለረጂም ሠዓታት መቀመጥን ተከትሎ የጉበት ስብ (ቅባት) በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋና ለጉበት ህመም እያጋለጠ መሆኑን አስገንዝበዋል። · የጉበት ፋት (ስብ፣ ቅባት) ለጉበት ህመም የሚያጋልጥበት ምክንያት ምንድን ነው? የጉበት ስብ በተለያዩ ሀገራት (በእኛም ሀገር በትላልቅ ከተሞች) በስፋት የሚከሰት ነው ያሉት ዶክተር ሚፍታህ፤ የጥናት ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከዓለም ሕዝብ 30 በመቶው (1/3ኛው ወይም ከ2 ቢሊየን በላይ ያህሉ) የጉበት ስብ ሊኖርበት ይችላል ይላሉ። በእርግጥ ሁሉም የጉበት ስብ ወደ ከፍተኛ የጉበት ቁስለት ይሸጋገራል ማለት እንዳልሆነ ገልጸው፤ የጉበት ስብ ካለባቸው መካከል ከ10 እስከ 15 በመቶ ያህሉ ብቻ ስቡ ከመብዛቱ የተነሳ ጉበቱን ማቁሰል እንደሚጀምር አስገንዝበዋል። ይህ ቁስለት ደግሞ እየዳነ እንደገና እያገረሸ ጠባሳ እየፈጠረ ይሄድና ጉበት ሥራውን ማከናወን የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ የጉበት መድከም ይከሰታል፤ ሰዎችም ጉዳት ይደርስባቸዋል ይላሉ። የጉበት ስብ መንስዔም፤ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ አለማድረግ (መቀመጥን ማዘውተር)፣ ፋስት ፉድ ማዘውተር (የተጠበሱ ምግቦች፣ በርገር፣ ችብስ፣ ዘይት የበዛባቸው ምግቦች) እንዲሁም ከፍተኛ ስኳር ያላቸው ለስላሳ መጠጦች፣ አልኮል መሆናቸውን አብራርተዋል። · የጉበት ስብን እንዴት መከላከል ይቻላል? የጉበት ስብ ከፍ እያለ ሲሄድ በአልትራሳውንድ እንደሚታይ (ትንሽ ከሆነ አይታም) የገለጹት ዶክተር ሚፍታህ፤ እስካሁን ክትባት እንደሌለው አረጋግጠዋል። ይህ ኬዝ እንቅስቃሴ ባለማድረግ፣ ኮምፒውተርም ሆነ ቴሌቪዥን ለማየት ረጂም ሠዓት በመቀመጥና በውፍረት መጨመር የሚከሰት መሆኑን ጠቁመው፤ መከላከያ መንገዱም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ (ቢያንስ በሳምንት እስከ 150 ደቂቃ በእግር መሄድ (ዎክ ማድረግ) ወይም በቀን ለ30 ደቂቃ ዎክ ማድረግ) መሆናቸውን ዘርዝረዋል። በተጨማሪም በፋብሪካ ፕሮሰስ የተደረጉ የታሸጉ ምግቦችን አለማዘውተር፣ ከስኳር ነጻ የሚሉ የሚበሉም ሆነ የሚጠጡ ነገሮችም ቢሆኑ በቀጥታም ባይሆን በሌላ መንገድ ጣፋጭ ስለሚኖራቸው አለማዘውተር፣ የተጠበሱ እንደ ችብስ እና መሰል ያሉ ምግቦችንም አለማዘውተር እንደሚገባ መክረዋል። ከልክ ያለፈ ውፍረት እንዳይኖር ማድረግም ለጉበት ስብ ተጋላጭነትን እንደሚቀንስ አስረድተዋል። · የጉበት በሽታ ምልክቶች እንደ ኬዙ ቢለያይም ጉበት 80 በመቶ ያህል ክፍሉ እስከሚጎዳ ምልክት ላያሳይ እንደሚችል ዶክተር ሚፍታህ ይገልጻሉ። 15 ወይም 10 በመቶ ጤናማ ክፍሉ ሲቀር (ከ85 በመቶ በላይ ክፍሉ በጣም ሲጎዳ) አንዳንድ ምልክቶች ሊያሳይ እንደሚችል ገልጸዋል። እነዚህ ምልክቶችም፤ ሆድ ላይ ውኃ መፍጠር (አሳይተስ)፣ ደም ማስመለስ መሆናቸውን እና በዚህ ወቅት የጉበት ንቅለ ተከላ ካልሆነ መፍትሔ እንደሌለው አንስተዋል። በአንጻሩ ግን፤ ‘አኪዩት ሄፓታይትስ’ የሚባለው ወይም አንድ ቫይረስ ጉበትን ሲያጠቃ ወዲያውኑ ሕክምና ይደረግለታል ሙሉ በሙሉም ይድናል ብለዋል።በዚህ ወቅት የሚየሳየው ምልክትም የዐይን ቢጫ መሆን፣ በቀኝ ደረት ሥር የውጋት ስሜት መኖር፣ ከፍተኛ ድካም መኖር፣ የምግብ ፍላጎት አለመኖር (ምግብ አስጠላኝ ማለት)፣ ማቅለሽለሽ እንዲሁም ማስመለስ መሆናቸውን አብራርተዋል። · የጉበት በሽታ አሳሳቢ ነው? የጉበት በሽታ በዓለም አቀፍ ደረጃም በተለያዩ ሀገራት ከ1 እስከ 10 ገዳይ (አሳሳቢ) ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል መሆኑን ዶክተር ሚፍታህ አስረድተዋል። በእኛ ሀገር ደረጃም የጉበት ካንሰር ከ3 እስከ 4 ገዳይ ተብለው ከሚጠቀሱ በሽታዎች መካከል መሆኑን ነው የጠቆሙት። በዓለም በየዓመቱ እስከ 3 ሚሊየን ሰዎች በጉበት በሽታ እንደሚሞቱ ገልጸው፤ ይህ አኃዝ አሳሳቢነቱን ያስረዳል ብለዋል። ምንም እንኳን ቀድሞ በሚወሰድ ክትባት (ለሄፓታይትስ ቢ) ከተከሰተ በኋላም በሚወሰድ መድኃኒት (ለሄፓታይትስ ሲ) አበረታች ውጤቶች ቢኖሩም፤ የጉበት ስብ (ቅባት) ግን በሀገራችንም ሆነ በዓለም ላይ በተለይም በከተማ ነዋሪዎች ዘንድ በስፋት እየተስተዋለ ያለ በመሆኑ አሳሳቢ ነው ብለዋል። · የጉበት በሽታ በተለይም በየትኞቹ የዕድሜ ክልሎች ላይ በስፋት ይከሰታል? የጉበት በሽታው ዓይነት በስፋት የሚከሰትበትን ዕድሜ እንደሚወስን ጠቁመው፤ በዚህም መሠረት ለምሳሌ፡- ሄፓታይትስ ቢ ከ30 ዓመት በታች ባሉ ሰዎች ላይ፣ ሄፓታይትስ ሲ ከ20 እስከ 40 ዓመት (አንዳንድ ጊዜ ከ40 ዓመት በላይ ባሉ ሰዎች ላይም ሊከሰት ይችላል)፣ የጉበት ስብ (ቅባት) ደግሞ ከ40 ዓመት በላይ ባሉ ሰዎች ላይ በስፋት እንደሚስተዋል ያስረዳሉ። · የጉበት በሽታን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? ዶክተር ሚፍታህ እንዳሉት የጉበት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የቻልባቸው የተለያዩ አማራጮች አሉ። ለምሳሌ፡- የሰውነት ክብደት (ውፍረት) ከልኩ እንዳያልፍ መቆጣጠር፣ ረጂም ሠዓት አለመቀመጥ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር፣ አልኮል አለመጠጣት (በቀን ከአንድ ቢራ በላይ መጠጣት ለጉበት ስብ ያጋልጣል)፣ ጣፋጭ ምግብና መጠጦችን መቀነስ (ጭራሽ አለመጠቀም ቢቻል)፣ ዘይት የበዛባቸውና የተጠባበሱ ምግቦችንም አለማዘውተር የሚሉትን አንስተዋል። በተጨማሪም በእኛ ሀገር ቀዳሚው የጉበት በሽታ ሄፓታይትስ ቢ መሆኑን በመግለጽ፤ ለዚህም ከ95 በመቶ በላይ የመከላከል ዐቅም ያለው ክትባት ስላለው ሦስት ጊዜ በመከተብ አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠዋል። · የሕክምና አማራጮች አሉት? ሄፓታይትስ ቢ ተከስቶ ጉበቱን ማቁሰል ከጀመረም የሚሰጥ ውጤታማ መድኃኒት መኖሩን አስታውቀዋል። ይህ መድኃኒት ምናልባት ዕድሜ ልክ ሊወሰድ ይችላል ነገር ግን ቁስለቱንም ሆነ ቫይረሱን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ነው ያሉት። ሄፓተይትስ ሲ ከሆነ ደግሞ በጣም ውጤታማ የሆነ ለሦስት ወር የሚሰጥ መድኃኒት አለ ብለዋል። ጠባሳ ከሆነ እና ከ85 በመቶ በላይ የሚሆነው የጉበት ክፍል ከተጎዳ (ከተበላሸ) ግን በውጭ ሀገር የጉበት ንቅለ ተከላ ማድረግ አስገዳጅ ይሆናል ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ ተላላፊ ካልሆኑ የጉበት በሽታዎች አንዱ እና አሁን በስፋት እየተስተዋለ ያለውን የጉበት ስብ (ቅባት) ጨምሮ የጉበት ጤናን ለመጠበቅ፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በየቀኑ ማድረግን መክረዋል። በዓመት አንድ ጊዜ የጤና ምርመራ በማድረግ ያሉበትን ሁኔታ ማወቅም ቢለመድ ሲሉ ይመክራሉ። በወቅቱ ከተደረሰብት የጉበት በሽታ መዳን እንደሚችል ገልጸው፤ በቸልተኝነት ወደ ተወሳሰበ ደረጃ ከፍ ካለ ግን እስከ ጉበት ካንሰር ሊደርስ እንደሚችልም አመላክተዋል።  
የጤና ነገር
Jun 24, 2026 2040
በዮሐንስ ደርበው የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ከተከሰተ በኋላስ የሚድንበት ዕድል ይኖራል? · ኪንታሮት እንዴት ይከሰታል? አጠቃላይ የቀዶ ጥገና ሐኪም የሆኑት ዶክተር ቤተልሔም አበራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በፊንጢጣ ውስጥ የሚገኙ በጤናማ መንገድ ፊንጢጣ እንዲዘጋ (‘ኩሽን’ እንዲሆን) የሚያደርጉ ደም ሥሮች በተለያየ ምክንያት ሲያብጡ ኪንታሮት (ሄሞሮይድ) ተከሰተ እንደሚባል አስረድተዋል። · የኪንታሮት በሽታ መንስዔ ይታወቃል? እንደ ሕክምና ባለሙያዋ ገለጻ ለኪንታሮት በሽታ መንስዔ ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል፤ የሰገራ ድርቀት በዋናነት ይነሳል። በተጨማሪም ይላሉ፤ በተለይም ሴቶች ላይ በእርግዝና ወቅት የጽንሱ መጠን (ክብደት) እየጨመረ በሚሄድበት ጊዜ ወደ መቀመጫ በሚያደርገው ጫና ምክንያት በፊንጢጣ ውስጥ የሚገኙ የደም ሥሮች እንዲያብጡ በማድረግ ለኪንታሮት መከሰት መንስዔ ይሆናል። በአሁኑ ጊዜ በስፋት ለሚከሰት የኪንታሮት በሽታ በመንስዔነት የሚነሳው ከመጠን ያለፈ ውፍረት መጨመር መሆኑንም ጠቁመዋል። ይህም ውፍረት ወደ መቀመጫ ጫና በማሳደር በፊንጢጣ ውስጥ ያሉ የደም ሥሮች እንዲያብጡ በማድረግ ኪንታሮት እንዲከሰት ያደርጋል ነው ያሉት። በሌላ በኩል እንደ ሥራ ባሕርያቸው ለረጂም ሠዓታት የሚቀመጡ ሰዎች ስለማይንቀሳቀሱና ይህን ተከትሎም ለድርቀት ስለሚጋለጡ ለኪንታሮት በሽታ ይዳረጋሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። ከአመጋገብ ዘይቤ ጋር በተያያዘም፤ በቂ ውኃ አለመጠጣት እና በፋይበር የበለጸጉ ምግቦችን አለማዘውተር ለድርቀት ስለሚዳርግ የኪንታሮት በሽታ እንዲከሰት ያደርጋል ብለዋል። ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) የጡት ካንሰርን መከላከል ይቻላል? · የኪንታሮት በሽታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ ያለው ለምንድን ነው? ኪንታሮት የተለመዱ (‘ኮመን’) ከሚባሉ የቀዶ ሕክምና በሽታዎች መካከል አንዱ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ቤተልሔም፤ በትክክል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን መረጃ ለጊዜው መግለጽ ባይቻልም በዓለም አቀፍ ደረጃ እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ የኪንታሮት ተጠቂ እንደሆነ ጠቁመዋል። እዚህ ላይ ልብ መባል ያለበት ጉዳይ የኪንታሮት በሽታ ከቦታ ቦታ ከሀገር ሀገር እንደሚለያይ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለዚህም ምክንያቱ ከውፍረት እና ለድርቀት ከሚያጋልጡ አመጋገቦች መዘውተር ጋር የተያያዘ በመሆኑ ነው ይላሉ። ለምሳሌ፡- በጣም ወፍራም ሰዎች በሚበዙባቸው እና ለድርቀት አጋላጭ ምግቦች በሚዘወተሩባቸው አካባቢዎች የኪንታሮት ተጋላጭነት ከፍተኛ ነው ይላሉ። የኪንታሮት በሽታ እየጨመረ (እየተስፋፋ) የሚሄድበት ምክንያትም ከአኗኗር ዘይቤ ጋር እንደሚያያዝ ገልጸው፤ ለምሳሌ አብዛኛውን ጊዜ ቁጭ ብሎ (ተቀምጦ) ማሳለፍ ለኪንታሮት አጋላጭ መንስዔ ነው ብለዋል። በተለይም ቢሮ አካባቢ የሚሠሩ ሰዎች ለበርካታ ሠዓታት ስለሚቀመጡ፣ ሥራ ሲበዛባቸውም ወደ መጸዳጃ ቤት መሄድ ባለባቸው ሠዓት ባለመሄድ (የሚሄዱበትን ጊዜ ስለሚያራዝሙ፣ ቆይ ይችን ልጨርስ…ትንሽ…የተወሰነ ደቂቃ እያሉ ማራዘም) ሰገራን ለድርቀት ያጋልጣል፤ ይህም የደም ሥሮች እንዲያብጡና ከፊንጢጣ ውጭ እንዲወጡ በማድረግ ለኪንታሮት መከሰት ያጋልጣል ብለዋል። · የኪንታሮት በሽታ ምልክቶች በፊንጢጣ ላይ ዕብጠት መኖር፣ መድማት፣ ማሳከክ እና የህመም ስሜት መኖር ከምልክቶቹ መካከል መሆናቸውን ዶክተር ቤተልሔም ያብራራሉ። የኪንታሮት በሽታ የውስጠኛው እና የውጨኛው ተብሎ እንደሚከፈል በመግለጽ፤ የበሽታው ደረጃም ከአንድ እስከ አራተኛ እንደሚመደብ ያስረዳሉ። ይህን ሲያብራሩም፤ በውስጠኛው የኪንታሮት በሽታ ባብዛኛው ህመም አይኖርም፣ የፊንጢጣ ደም ሥሮች ዕብጠትና መድማት ይኖራል፤ በውጨኛው የኪንታሮት በሽታ ግን የህመም ስሜት ይኖራል ይላሉ። · የኪንታሮት በሽታ ደረጃዎች ደረጃዎቹን በተመለከተ ሲያስረዱ፤ ምልክቶቹን እንዳስተዋሉ ቶሎ ወደ ሕክምና ባለመሄድ ከአንደኛ ወደ ሁለተኛ ከዚያም ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ እየተባባሰ እንደሚሸጋገር ገልጸዋል። ስለዚህ ሰዎች ምልክቶቹን እንዳዩ ቢታከሙ ደረጃው ከፍ ሳይል በሽታውን የመግታት ዕድል ይኖራቸዋል ነው የሚሉት። የመጀመሪያ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በዚህ ወቅት የኪንታሮት ህሙማን እንኳን የዕብጠቱን መኖር ባብዛኛው በእጃቸውም ነክተው እንደማያውቁት እና የመድማት ምልክት ሊኖር እንደሚችል ተናግረዋል። ሁለተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በዚህኛው ደረጃ ደግሞ ህሙማኑ በሚጸዳዱበት ወቅት ዕባጩ ወደ ውጭ እንደሚወጣ እና ሲጨርሱ በራሱ ጊዜ ዕባጩ ወደ ቦታው እንደሚመለስ አስገንዝበዋል። ሦስተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በሽታው ያለባቸው ሰዎች በሚጸዳዱበት ወቅት ወደ ውጭ የሚወጣውን ዕባጭ በእጃቸው ወደ ውስጥ ካላስገቡት በራሱ ጊዜ የማይመለስበት ደረጃ መሆኑን ይገልጻሉ። አራተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ ይህ ደረጃ ዕባጩ ከፊንጢጣ ውጭ ይወጣና ተገፍቶም ወደ ውስጥ መግባት የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታ፤ ያለ ቀዶ ሕክምና ሰዎች እቤታቸው እንዲያደርጉ የሚመከሩትን ሁኔታዎች በአግባቡ ካደረጉ ወደ ቀጣዩ ደረጃ እንዳይሸጋገር ማድረግ ይቻላል ይላሉ። · በወቅቱ ካልታከመ በአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ኪንታሮትን ከላይ በተገለጹ የኑሮ እና አመጋገብ ዘይቤዎች ማስተካከል እንደሚቻል (ወደ ቀጣዮቹ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ሳይሸጋገር ባለበት እንዲቆይ) ማድረግ እንደሚቻል ያስረዳሉ። ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ከደረሰ ግን የቀዶ ሕክምና እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ ይህ ደግሞ ጥቅምም የጎንዮሽ ጉዳትም እንዳለው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም በመጀመሪያዎቹ ደረጃዎች ካልታከመ እና ወደ መጨረሻዎቹ ደረጃዎች ከደረሰ ከፍተኛ የደም መፍሰስ እንደሚኖረውና ይህም ከሰው ደም እስከመለገስ ሊያደርስ እንደሚችል ይገልጻሉ። ወደ ውጭ ወጥተው በሚቀሩ የፊንጢጣ ደም ሥሮች ውስጥ የደም መርጋት ሊያጋጥም እንደሚችልና ይህም ከፍተኛ ህመም እንደሚያመጣ ተናግረዋል። በዚህም ድንገተኛ ሕክምና የመፈለግ ደረጃ ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ነው ያመላከቱት። · የኪንታሮት በሽታ ሙሉ በሙሉ ይድናል ወይስ አይድንም? በየትኛውም ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታ በጊዜውና በአግባቡ ከታከመ ሙሉ በሙሉ እንደሚድን ዶክተር ቤተልሔም አረጋግጠዋል። በተለይም አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታን ሰዎች እቤታቸው በሚያደርጉት ትሪትመንት (የአኗኗርና አመጋገብ ዘይቤያቸውን በማስተካከል) ሊያድኑት እንደሚችሉም አመላክተዋል። በተጨማሪም ወደ ሕክምና ተቋም ቢሄዱ፤ የሰገራ ማለስለሻ፣ ፊንጢጣ ላይ የሚቀባ የህመምና ዕብጠት መቀነሻ መድኃኒት እንደሚሰጥ በመግለጽ ይህ ከተስተካከለ የአኗኗር ዘይቤያቸው ብሎም በብዛት ውኃ ከመጠጣት ጋር ሲሠናሰል በመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ኪንታሮት የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህንን አልፎ ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ላይ ቢደርስ እንኳን የተለያዩ የቀዶ ሕክምና አማራጮች እንዳሉ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት እንደ ኪንታሮቱ መጠን ‘ረበርባንድ’ (ዕባጩን ዙሪያውን በመቋጠር በጊዜ ሂደት ደርቆ እንዲረግፍ የማድረግ ሕክምና) እና ኪንታሮቱን (የደም ሥሮቹን ዕባጭ) በቀጥታ በቀዶ ሕክምና በማውጣት ማከም ይቻላል፤ መዳንም ይቻላል ብለዋል። · ኪንታሮት እና ባሕላዊ ሕክምና ከላይ እንደገለጽነው (የኑሮ ዘይቤን ማስተካከል፣ ውኃ በብዛት መጠጣት፣ በፋይበር የበለጸጉ ምግቦችን ማዘውተር፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ) ከዚያም ዘመናዊ ሕክምና መከታተል ተገቢ መሆኑን የሕክምና ባለሙያዋ መክረዋል። በአንጻሩ በባሕል (በልማድ) ፊንጢጣ ውስጥ የሆነ ነገር መቅበር፣ ኪንታሮትን በግለት መተኮስ ለካፋ ችግር ሊያጋልጥ ስለሚችል ይህን ከማድረግ መቆጠብ ይመከራል ብለዋል። ምክንያቱም ለፊንጢጣ መጥበብ (በሚጸዳዱበት ጊዜ ለመሰንጠቅና መድማት) ብሎም ለመሰል የጎንዮሽ ጉዳቶች ሊዳርግ እንደሚችል አስረድተዋል። ኪንታሮት በአግባቡ በቀዶ ሕክምና ካልወጣ በባሕል (ልማድ) መነካካቱ ለባክቴሪያ እንደሚያጋልጥ፤ ባክቴሪያው ደግሞ ከፊንጢጣ አልፎ ወደ ሌሎች የሰውነት ክፍሎች (ለምሳሌ ወደ ታፋና አካባቢው) የሚዛመት መግል የያዘ ከፍተኛ ኢንፌክሽን ያጋልጣል ብለዋል። በዚህ ጊዜ ወደ ሕክምና ሲመጡ ሕክምናውን በጣም ከባድ (ውስብስብና አስቸጋሪ) ያደርገዋል ነው ያሉት። · የፊንጢጣ ካንሰርና የኪንታሮት በሽታ ቀደም ብለን እንዳነሳነው የኪንታሮት በሽታ ምልክቶች፤ ማሳከክ፣ ዕባጭ፣ መድማት እና ህመም ናቸው ያሉት ዶክተር ቤተልሔም፤ የፊንጢጣ ካንሰርም ተመሳሳይ ምልክቶች ይኖሩታል ይላሉ። ስለዚህ ማንኛውም ሰው በፊንጢጣ በኩል ደም ሲመለከት ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም እንዲሄድ መክረዋል። ምክንያቱም ይላሉ፤ በፊንጢጣ በኩል ደም የሚታየው አንድም በኪንታሮት በሽታ እንዲሁም በአንጀት ቁስለት፣ በፊንጢጣ ካንሰር፣ በጨጓራ ቁስለት እና በትልቁ አንጀት ካንሰር ምክንያት ሊሆን ስለሚችል ነው። ከመድማት በተጨማሪ የፊንጢጣ ቁስለት በስፋት ከታየ ካንሰር ሊሆን እንደሚችልም አመላክተዋል። ቁስለቱ ፊንጢጣ ውስጥ ስለሚሆን በእጅ መንካትና ማወቅ የማይቻልበት ሁኔታ እንደሚኖርም ጠቁመዋል። · ምክረ ሐሳብ ለኪንታሮት በሽታ ላለመጋለጥ ወይም ከመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ወደ ቀጣዮቹ ደረጃዎች እንዳይሸጋገር መንስዔዎቹን መቀልበስ ተገቢ መሆኑን በአጽንዖት አንስተዋል። በዚህም መሠረት ድርቀት እንዳይኖር ማድረግ ቀዳሚው መፍትሔ መሆኑን አስገንዝበዋል። ለዚህም በቂ ውኃ መጠጣት፣ ከ25 እስከ 30 ግራም ፋይበር በየቀኑ መውሰድ (በደንብ ፋይበር ያላቸው ምግቦችን መመገብ ለምሳሌ፡- ጎመን፣ ቆስጣ፣ ብርቱካን፣ ሙዝ፣ አፕል፣ ባቄላ፣ ገብስ፣ አጃ፣ ስንዴ) ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም ድርቀትን ለመከላከል ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባ በመግለጽ፤ በሥራ ባሕርያቸው ቢሮ ውስጥም ሆነ ሌላ ቦታ መቀመጥ የሚያበዙ ሰዎች በመሐል በመነሳት መንቀሳቀስ እንዲሁም ከሥራ ሲወጡ በእግር መሄድ (ዎክ ማድረግ) እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ማድረግ ለአንጀት እንቅስቃሴ ዕገዛ በማድረግ ድርቀት እንዳይኖር ይጠቅማቸዋል ብለዋል። ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያለባቸው ሰዎችም ክብደታቸውን እንዲቀንሱ መክረው፤ ይህ ሲሆን ከፊንጢጣ ውጭ የነበረው የደም ሥር ዕብጠት (የኪንታሮት በሽታ) ወደ ነባር ቦታው እንዲመለስ ወይም ባለበት እንዲቆይ (በይበልጥ ተገፍቶ እንዳይወጣ) ይረዳል ይላሉ። ከልማዳዊ ሕክምና በመራቅ ዘመናዊ ሕክምናን ቀዳሚ ምርጫ ለማድረግ በተለይም ቀድሞ መከላከል የሚቻልበትን ብልኀት ለማዳበር ስለ ኪንታሮት በሽታ በስፋት ግንዛቤ መፍጠር ተገቢ ነው ይላሉ። በፊንጢጣ በኩል ደም ሲታይ ሁሌም ኪንታሮት ላይሆን እንደሚችልና ካንሰር ሊሆን እንደሚችልም በመገንዘብ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ ወደ ሌሎች ደረጃዎች ሳይሸጋገር በማከም እንዲድን ማድረግ ተገቢ መሆኑን መክረዋል።
ትንታኔዎች
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 3143
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው  
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 4522
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ።   ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…! 
Jun 15, 2026 2934
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 8295
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 4507
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 17554
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 10621
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 16382
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 90748
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 70189
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 50401
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 47959
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 35617
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 35121
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 34583
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 33775
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 90748
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 70189
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 50401
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 47959
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 1191
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ልዕልና በአረንጓዴው ከፍታ
Jun 25, 2026 1657
(በዮርዳኖስ ዓባይነህ) የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ለማልማት የጀመረችው ታሪካዊና አርአያነት ያለው ብሔራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ዘመቻ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ አዋቂዎችና ልዩ ልዩ ተቋማት በነቂስ በመውጣት በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በከፍተኛ የሕዝብ ንቅናቄና በአንድነት መንፈስ ለመትከል ችለዋል። በዚህ ተከታታይ የችግኝ ተከላና እንክብካቤ ሥራ ምክንያት ለዓመታት ተራቁተው የነበሩ ተራራማና ኮረብታማ ቦታዎች እንዲሁም የሀገሪቱ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያገግም ሆኗል፤ ይህም የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ የከርሰ-ምድር ውሃ መጠን እንዲጨምር ተጨባጭ አስተዋጽኦ አበርክቷል። አካባቢን ከመጠበቅ ባሻገር፣ መርሃ-ግብሩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የፍራፍሬ፣ የቡናና የቅመማ ቅመም ችግኞችን በማካተት አርሶ አደሩ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝና የምግብ ዋስትናው እንዲረጋገጥ ትልቅ የኢኮኖሚ በር ከፍቷል። በተጨማሪም በዋና ዋና ከተሞች የተገነቡት ውብ አረንጓዴ ፓርኮች ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ንጹህና ማራኪ ከማድረጋቸውም በላይ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ እየሆኑ ይገኛሉ። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ለአሁኑ ትውልድ የኢኮኖሚ ዋስትናን፣ ለወደፊቱ ደግሞ የተስተካከለ የአየር ንብረትና ለምለም ሀገርን የሚያስረክብ ታላቅ የትውልድ ቅርስ በመሆኑ፣ የተተከሉትን ችግኞች ተንከባክቦ ማሳደግና ዘላቂነታቸውን ማረጋገጥ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ነው። 👉ከተፈጥሮ ጋር የተጻረረው የሰው ልጅ ስልጣኔ የሰው ልጅ በምድር ላይ መኖር ከጀመረበት ጥንታዊ ዘመን አንስቶ በሕይወት ለመቀጠልና ሕልውናውን ለማረጋገጥ ከተፈጥሮ ብሎም ከመሰሎቹ ጋር ጠንካራ እና ቀጣይነት ያለው መስተጋብር ሲያደርግ ቆይቷል። ነገር ግን ይህ መስተጋብር ሚዛኑን እየሳተ መጥቶ፣ ከጥንቱ የግብርና ስልጣኔ እስከ ዛሬው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ድረስ በሰው ልጅ እጅ የተፈጸመው የተፈጥሮ መራቆት በምድር ላይ ከባድ ጠባሳ ጥሏል። የደን መጨፍጨፍ፣ የአፈር መሸርሸር እና የውሃ አካላት መናመን የዚሁ አውዳሚ ጉዞ ውጤቶች ናቸው። አግባብ ያለው የአካባቢ ጥበቃ ባለመደረጉም፣ በቢሊዮን የሚቆጠሩ አዕዋፋትና የዱር እንስሳት ለዘመናት ከኖሩበትና ለነሱ ከሚስማማቸው ቀያቸው ለመሰደድ ተገድደዋል። የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና ግብርና ድርጅት (FAO) በ2016 እ.ኤ.አ ባወጣው ጥናት መሠረት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ 92 ሺህ ሄክታር ደን ይጨፈጨፋል። ለዚህም የእርሻ መሬት ማስፋፋትና የማገዶ ፍላጎት መጨመር በዋና ምክንያትነት ይጠቀሳሉ። ይህ የዓለም አቀፍ ስጋት ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ደግሞ የራቀ ሳይሆን የውስጥ ቁስል ነበር። በደን መጨፍጨፍና በአፈር መሸርሸር ምክንያት በተደጋጋሚ የተከሰቱት የድርቅ፣ የረሃብ፣ የመሬት መንሸራተት እና የሕዝቦች መፈናቀል ታሪኮች የቅርብ ጊዜ ትዝታዎቻችን ናቸው። 👉የ"ክፉ ቀን" ትርክት እና የስነ-ልቦና ጠባሳ ከ1888 እስከ 1892 እ.ኤ.አ በሀገራችን የተከሰተውና '’ክፉ ቀን'’ ተብሎ የሚታወቀው አሰቃቂ የረሃብ ታሪክ ፣ ከዚያም በኋላ በወሎና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የታዩት ድርቆች በዓለም መገናኛ ብዙሃን ጎልተው ሲዘገቡ ቆይተዋል። ይህ አሳዛኝ ክስተት ለውጭ መገናኛ ብዙሃንና ተቋማት ተጨማሪ ዝና እና ገቢ ማግኛ ሰበብ ሲሆን፣ ለሕዝባችን ግን ለዘመናት ያልተሻረ የስነ-ልቦና ቁስል ጥሎ አልፏል። ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ የድህነት እና የረሃብ ተምሳሌት አድርጎ በመሳል፣ ኢትዮጵያውያንን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን አንገት ያስደፋ ጥቁር ታሪክ ሆኖ ኖሯል። ታዲያ ይህንን የውርደት ትርክት የሚቀይር፣ ሀገራዊ ክብርን የሚመልስና ቀጣይነት ያለው የአካባቢ ጥበቃን የሚያረጋግጥ ወሳኝ እርምጃ መውሰድ የህልውና ጉዳይ ነበር። 👉አረንጓዴ አሻራ፦ ተግዳሮቶችን የመለወጥ የፅናት ጉዞ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት፣ በተቋማት ቅንጅትና በተደራጀ የሕዝብ ንቅናቄ "የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር" ተጀመረ። በመጀመሪያው ዓመት “40 ዛፎች በነፍስ ወከፍ” በሚል መሪ ሃሳብ የተጀመረው ዘመቻ፣ ከዕቅድ በላይ 18 በመቶ ስኬት በማስመዝገብ የሕዝቡን የልማት ጥም አሳየ። በሁለተኛው ዓመት (2012 ዓ.ም) ዓለምን ያሸበረው የኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ወረርሽኝ ቢከሰትና ማኅበራዊ መራራቅ፣ ጥንቃቄዎች እንዲሁም ከቤት ሆኖ መሥራት ግዴታ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያውያን የአረንጓዴ ጉዞ አልተገታም። “እየተጠነቀቅን እንተክላለን” በሚል መሪ ሐሳብ ፣ ማኅበረሰቡ ደህንነቱን ጠብቆ በመንቀሳቀሱ ከዕቅድ በላይ 14 በመቶ ችግኝ መትከል ተችሏል። 👉የሰባት ዓመታት ስኬቶች በቁጥር እና የስነ-ምህዳር መነቃቃት ይህ ስራ ለአንድና ለሁለት ዓመት የተደረገ ዘመቻ ሳይሆን የሰባት ዓመታት ተከታታይ የፅናት ጉዞ ነበር። ከ2011 እስከ 2017 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በኢትዮጵያ ምድር ላይ ተተክለዋል። የችግኞቹ የስብጥር ይዘትም ስልታዊ የደን ልማትን ያሳያል፦ 60 በመቶ የጥምር እርሻ ደን (Agroforestry) 35 በመቶ የተፈጥሮ ደን ሽፋን 5 በመቶ የከተማ ውበት ዛፎች ከተከናወኑት የክትትልና ቁጥጥር ሪፖርቶች መረዳት እንደሚቻለው፣ ከተተከሉት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥ በአማካይ ከ75 በመቶ እስከ 80 በመቶ በላይ የመፅደቅ መጠን (Survival Rate) ማሳየት መቻላቸው የሥራውን ውጤታማነት በተጨባጭ ያረጋግጣል። ይህ መጠነ-ሰፊ ስራ ቀደም ሲል ከ2010 እስከ 2016 ዓ.ም ይከሰት የነበረውን የደን መጨፍጨፍ በ65 ሺህ ሄክታር በመቀነስ፣ የሀገሪቱን የደን ሽፋን በ11 ነጥብ 4 በመቶ ከፍ እንዲል አድርጓል። የተከናወነው የተቀናጀ የልማት ስራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስና የውሃ አካላትን በማንሰራራት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ይህ የደን ሽፋን ዕድገት ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከካርቦን ሽያጭ (Carbon Trading) እና ከአየር ንብረት አረንጓዴ ፋይናንስ (Green Finance) ልታገኝ የምትችለውን የኢኮኖሚ ዕድል በከፍተኛ ደረጃ የሚያሰፋላት ነው። 👉ከስነ-ምህዳር ጥበቃ ወደ ቢሊዮን ዶላር ኢኮኖሚ ግንባታ እና የኮሪደር ልማት የአረንጓዴ አሻራ ስኬት ስነ-ምህዳሩን በማደስ ብቻ አልተገደበም፤ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንትም ጭምር ቀይሯል። መሬትን የማከምና የአፈር እርጥበትን የመመለስ ስራው በ2017 ዓ.ም 280 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ በሀገር ውስጥ ለማምረት አስችሏል። ይህ ውጤት ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ለስንዴ ማስመጫ ታወጣ የነበረውን አንድ ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ያስቻለ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው። በተጨማሪም ይህ አረንጓዴ ልማት ኢትዮጵያን በአፍሪካ 2ኛዋ የአቮካዶ ምርት ላኪ ሀገር ያደረጋት ሲሆን፣ በ2017 ዓ.ም የቡና ምርትን በማስፋፋትና ጥራትን በመጨመር 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ታሪካዊ የውጭ ምንዛሪ ለማስመዝገብ አስችሏል። ይህ ታላቅ ስኬት የተገኘው የኢኮ-ሲስተም ልማትን፣ የገጠር ልማትን፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትን እና የከተማ ኮሪደር ልማትን (Urban Corridor Integration) ባካተተ የተቀናጀ ስትራቴጂ ነው። በተለይም በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ከመቀየር ባለፈ፣ ለነዋሪዎች ምቹና ሰፊ የእግር መንገዶችን፣ ማራኪ የአረንጓዴ ስፍራዎችንና መናፈሻዎችን በመፍጠር ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች ደህንነቱ የተጠበቀና ማራኪ የከተማ ቱሪዝም (Eco-tourism) መዳረሻዎችን በተግባር መፍጠር ችሏል። 👉የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ መሪነት እና ዓለም አቀፍ እውቅና ይህ ንቅናቄ በሀገር ውስጥ ካለው ፋይዳ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ "የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ" መሪ እንድትሆን አድርጓታል። እንደ ኤርትራ፣ ጅቡቲ፣ ፓኪስታን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሩዋንዳ ያሉ ሀገራት ከኢትዮጵያ ተሞክሮ በመቅሰም በሀገራቸው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር መጀመራቸው የዚህ ማሳያ ነው። በተጨማሪም የዓለም ምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"አግሪፎድ ሻምፒዮን" እና "የላቀ የአፍሪካ አመራር ሽልማት" መስጠቱ ፣ ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ምግብ ጉባኤን ማስተናገዷ እና በ80ኛው የፋኦ ጉባኤ ላይ ለሀገሪቱ አጠቃላይ ዕድገት የተሰጠው እውቅና የዓለምን አድናቆት ያረጋገጡ ክስተቶች ናቸው። እነዚህ ዓለም አቀፍ ምስክርነቶች ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ተስሎባት የነበረውን የድርቅ እና የረሃብ አፍራሽ ትርክት በአረንጓዴ ልማት፣ በአንድነት እና በምርታማነት በተግባር የቀለበሰችበት ታላቅ ድል ነው። 👉ስምንተኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ፡ "ተስፋን እንትከል!" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ማስጀመራቸው ይታወቃል። መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልፅግና አሰናስሎ የሚያረጋግጥ ብሔራዊ የልማት አቅጣጫ መሆኑ ተመስክሮለታል። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ዘመቻ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ መጀመሩ ጥልቅ ትርጉም አለው። ተስፋ የነገን ብሩህ ምዕራፍ ዛሬ ላይ ለመጻፍ የሚያስችል አረንጓዴ መቀነት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉትም፤ አረንጓዴ ዐሻራ አፈራችንን ከስደት፣ የታላቁን ህዳሴ ግድባችንን ደግሞ ከደለል የሚታደግ ብሔራዊ ጋሻ ሆኗል። የአባቶቻችን የዓድዋ ድል ወራሪን ያሳፈረ ታላቅ ገድል እንደነበረ ሁሉ፣ የአሁኑ ትውልድ በአረንጓዴ ዐሻራ እያከናወነ ያለው ተግባርም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አዲስ የታሪክ ገድል እየሆነ ይገኛል። ይህ ንቅናቄ የሀገሪቱን የተረጂነት ታሪክ ወደ ማድረግና ራስን ወደ መቻል ዘመን የሚያሸጋግር የመደመር መርህ መገለጫ ነው። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ ቁጥራዊ መረጃዎች የህዝብ ቁርጠኝነት ማሳያ ናቸው። ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል። በዘንድሮው መርሃ ግብር ደግሞ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን፤ ይህም አጠቃላይ የተተከሉትን ችግኞች ቁጥር ወደ 56 ቢሊየን ያደርሰዋል። ይህ ታላቅ ስኬት እዚህ ላይ አያበቃም፤ ሀገሪቱ በፈረንጆቹ 2029 የሚካሄደውን የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) ስታስተናግድ፣ በአጠቃላይ 65 ቢሊየን ችግኞችን መትከል የቻለች መሪ ሀገር መሆኗን ለዓለም የምታበስርበት ታሪካዊ ምዕራፍ ይሆናል። በክረምቱ ወራት እያንዳንዱ ዜጋ "ተስፋን በመትከል" የዓድዋን የኩራት ስሜት በአረንጓዴ ልማት ሊደግመው ይገባል። የበለፀገችና የተከበረች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ፣ የተተከሉትን ችግኞች ተንከባክቦ ማሳደግና የአረንጓዴ ዐሻራን ስኬት ማስፋትና ማስቀጠል የዛሬው ትውልድ የማይታጠፍ ብሔራዊ ጥሪ ነው። 👉የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች በኢትዮጵያ እስከአሁን የተመዘገቡ ስኬቶችን ዘላቂ ለማድረግና የተፈጥሮ ቅርሶቻችንን ይበልጥ ለማጠናከር የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎች በግልጽ ተቀምጠዋል። መንግሥት የልማቱን የሕዝብ ባለቤትነት ማረጋገጥና ማቀናጀት፣ አረንጓዴ ልማትን እንደ ባህል መገንባት፣ የቴክኖሎጂ እሴቶችን በመጠቀም የሥራ ዕድሎችን ማስፋፋት፣ በተፈጥሮ ሀብት ላይ የሚደረገውን ጫና መቀነስ፣ እንዲሁም አዲስ የተገነቡ የኮሪደር ልማቶችንና ፓርኮችን በመጠበቅ የጎብኝዎችን ደህንነት ማረጋገጥና የተፈጥሮ ቅርስን አብሮ ማጠናከር ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጧል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም