ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ካፍ የኢትዮጵያ እና የሳኦቶሜና ፕሪንሲፔ ጨዋታን 10 ሺህ ተመልካች ስታዲየም ተገኝቶ እንዲከታተለው ወሰነ
Mar 30, 2026 13
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሳኦቶሜና ፕሪንሲፔ አቻው ጋር የሚያደርገውን የ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ 10 ሺህ ተመልካች በድሬዳዋ ስታዲየም ተገኘቶ እንዲከታተለው መወሰኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። ካፍ የነገው የኢትዮጵያ እና ሳኦቶሜ ጨዋታ በዝግ እንዲካሄድ ውሳኔ አሳልፎ ነበር። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በስታዲየሙ ዙሪያ የተሰጡ የግምገማ አስተያየቶችን መሰረት በማድረግ በፍጥነት ለማስተካከል እርምጃ መውሰዱን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ከከተማ አስተዳደሩ እርምጃ ጎን ለጎን ጨዋታው ለተመልካች ክፍት እንዲሆን ባደረገው ከፍተኛ ጥረት እንዲሁም የካፍ ሴኪዩሪቲ ኦፊሰር በአካል ተገኝተው ከገመገሙ በኋላ በላኩት ሪፖርት መሰረት ካፍ 10 ሺህ ተመልካች በስታዲየም ተገኝቶ እንዲከታተል ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል። የሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታ ነገ ከቀኑ 10 ሰዓት በድሬዳዋ ስታዲየም ይካሄዳል።
በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ በእናቶች ላይ የሚከሰት የጤና እክልን ለመከላከል ትኩረት ተደርጓል
Mar 30, 2026 29
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ በእናቶች ላይ የሚከሰትን የጤና እክል ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። የጤና ሚኒስቴር በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ ከሚከሰቱ ጤና ችግሮች መካከል አንዱ የሆነው የአዕምሮ ጤና እክል የሚያጋጥማቸውን እናቶች ጤና መጠበቅ ላይ ትኩረት ያደረገ አውደ ጥናት አካሂዷል። በቤልጂየም ትሮፒካል ሜዲሲን ኢኒስቲትዩት፣ በአዲስ አበባና ጎንደር ዩኒቨርስቲዎች ትብብር የተዘጋጀው አውደ ጥናትም የአዕምሮ ጤና እክል የሚጋጥማቸውን እናቶች የጤና ደረጃና የመፍትሔ እርምጃዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በጤና ሚኒስቴር የፖሊሲ፣ ስትራቴጂና ምርምር መሪ ሥራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር አስቴር ጸጋዬ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ የእናቶችና ህጻነትን ሞት ለመቀነስ የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል። እናቶች በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ የሚያጋጥማቸው የአዕምሮ ጤና እክልም ትኩረት የሚፈልግ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል። በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ ለሚከሰት የአዕምሮ ጤና እክል ተጋላጭነትን ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ለዚህም የባለድርሻ አካላት፣ ከፍተኛ የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ተቋማት ቅንጅት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። በጤና ሚኒስቴር ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችና የአዕምሮ ጤና ዴስክ ኃላፊ ዶክተር ሰላማዊት አየለ፤ በእርግዝናና ከወሊድ በኋላ ከቀላል እስከ ከባድ የሚደርስ የአዕምሮ ጤና እክል የሚያጋጥማቸው እናቶችን በተመለከተ በማህበረሰቡ ዘንድ በተሳሳተ ግንዛቤ ችግሩን ተፈጥሯዊ አድርጎ ይወሰዳል። ይህም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተጋላጭነታቸውን እንደሚያባብስ አስረድተው፤ ለዚህም በጤና ባለሙያዎች የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በቤልጂየም ትሮፒካል ሜዲሲን ኢኒስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር አንተነህ አሰፋ እንደገለጹት፤ የእናቶችን በእርግዝናና ከወሊድ በኋላ የጤና ችግሩን ለመቀነስ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በዘርፉ የመጡ ውጤቶችን በማስቀጠል የጥናትና ምርምር እንዲሁም የዲጂታል ቴክኖሎጂ የትብብር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ የፍትህ ስርዓቷን በዓለም አቀፍ አጋርነት ለማዘመን ቁርጠኛ ናት
Mar 30, 2026 28
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የፍትህ ስርዓቷን ጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት በመፍጠር ለማዘመን በቁርጠኝነት ትሰራለች። በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዓለምአንተ አግደው የተመራ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልዑክ በኔዘርላንድስ ሄግ ስትራቴጂካዊ የስራ ጉብኝት እያደረገ ነው። ልኡኩ ከፍተኛ እውቅና ካላቸው ዓለም አቀፍ የህግ ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያካሄደ ይገኛል። ልዑኩ ከዓለም አቀፉ ቋሚ የግልግል ዳኝነት ፍርድ ቤት (Permanent Court of Arbitration) እና ከሄግ ዓለም አቀፍ የሕግ አካዳሚ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋርም ተወያይቷል። የውይይቶቹ ዋነኛ ትኩረትም በኢትዮጵያ በተለይም በአማራ ክልል እየተከናወነ ለሚገኘው የፍትህ ዘርፍ ማሻሻያ ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከርና ቴክኒካዊ ድጋፎችን ማግኘት እንደሆነ ተመላክቷል። ጉብኝቱ ኢትዮጵያን በቀጣናው የግልግል ዳኝነት ማዕከል የማድረግ አካል ሲሆን በአማራ ክልል ዘመናዊ እና ማዕከላዊ የፍትህ ተቋምን የመገንባት እቅድ ተሞክሮ የመውሰድ ውጥንም ያለው ነው። ከፍተኛ ባለስልጣናቱ በውይይቶቹ ላይ ኢትዮጵያ በጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት የሕግ እና ዳኝነት ስርዓቷን ለማዘመን ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸዋል። በተጨማሪም ልዑኩ በሄግ የሚገኘውን ታሪካዊ የሰላም ቤተ መንግስት (historic Peace Palace) የጎበኙ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያ የፍትህ ዘርፍ የማሻሻያ ጉዞ አስመልክቶ ልምድ የተቀሰመበት እንደሆነም ተመላክቷል። ጉብኝቱ ኢትዮጵያ ያላትን ዓለም አቀፍ የሕግ ትስስር እና የፍትህ ዘርፍ ሪፎርሙን ወደፊት ለማራመድ የሚያስችል እርምጃ መሆኑ ተገልጿል። በውይይቶቹም ከአቶ አለምአንተ አግደው በተጨማሪ በቤልጅየም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ፍርቱና ዲባኮ ፣ የኢትዮጵያ ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ማኔጅንግ ዳይሬክተር ኢንጂነር አንዋር ካሳሁን እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሙዎች ተሳትፈዋል።
ባስመዘገብነው የመጀመሪያ ድል ሳንዘናጋ የመልሱን ጨዋታ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንገባለን - አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ
Mar 30, 2026 60
ድሬዳዋ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ላይ ባገኘው ድል ሳይዘነጋ የመልሱን ጨዋታ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንደሚገባ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ተናገሩ። አሰልጣኝ ዮሐንስ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ የሚደረገውን የመልስ ጨዋታ አስመልክቶ ዛሬ በድሬዳዋ ስታዲየም ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። አሰልጣኙ በመግለጫቸው ዋልያዎቹ የቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታን ለማሸነፍ የሚያስችላቸውን ዝግጅት አድርገዋል ሲሉ ገልጸዋል። ዋልያዎቹ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ሞሮኮ ላይ ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ 3 ለ 0 ማሸነፋቸውን አስታውሰው፤ ይህ ውጤት በምንም መንገድ መዘናጋት ሳይፈጥር ነገ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንገባለን ብለዋል። የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች በጥሩ የማሸነፍ መንፈስ ታጅበው እንደሚጫወቱ ተናግረዋል። ተጫዋቾቹ በቂ ልምምድ ማካሄዳቸውንና በስነ-ልቦናም ጭምር ማሸነፍ የሚያስችላቸውን ዝግጅት ማድረጋቸውንም ነው የገለጹት። በአባቱ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት በመጀመሪያው ጨዋታ ያልነበረው የቡድኑ አምበል ጋቶች ፓኖም ለመልሱ ጨዋታ ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር በመቀላቀል ልምምድ ማድረጉን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ነገ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር የሚካሄደውን የ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ካሸነፈ ወደ ምድብ ድልድሉ ይቀላቀላል። 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምስራቅ አፍሪካ አገራት በሆኑት ኬንያ፣ ታንዛኒያ እና ዩጋንዳ ጣምራ አዘጋጅነት እ.አ.አ ጁን 2027 ይካሄዳል።
የአፋር ክልልን የቱሪስት መዳረሻዎች የበለጠ ለማልማት እና ለማስተዋወቅ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Mar 30, 2026 102
ሰመራ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ክልል የቱሪስት መዳረሻዎችን የበለጠ ለማልማት እና ለማስተዋወቅ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ። የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማስተዋወቅና በማልማት ረገድ ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል። የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ሁመድ እንደገለጹት የተደረገው ስምምነት ዘርፉን የበለጠ ለማስተዋወቅና ለማልማት ትልቅ እገዛ ያደርጋል። ስምምነቱ የአፋር ክልልን የቱሪዝም መዳረሻዎች ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችሉ በምርምር ላይ የተመሰረቱ ሥራዎችን ለማከናወንም ያግዛል ብለዋል። ቢሮው ዘርፉን የበለጠ ለማሳደግ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅት የሚያጠናክሩ እንቅስቃሴዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም በዘላቂነት ለማሳደግ የሚያስችል አሰራር ለማዘመን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መሐመድ ኡስማን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚቆየው ስምምነቱ የአፋርን ክልል ቱሪዝም ለማሳደግ ቁልፍ መሆኑን ጠቁመዋል። ዩኒቨርሲቲው ሁሉን አቀፍ የቱሪዝም ልማት ስትራቴጂ ማዘጋጀት፣ የቱሪስት መስህብ መረጃዎችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ ማድረግ እንዲሁም ዘመናዊ የቱሪስት መዳረሻ ካርታ እና የማስተዋወቂያ ሥራዎችን ያከናውናል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ ስምምነቱ የቱሪዝም ልማትን በምርምር ሥራዎች በመምራት ዓለም አቀፍ ደረጃውን እንዲጠብቁ ለማድረግም እንደሚያግዝ አመልክተዋል።
ፖለቲካ
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ሃይል ወታደራዊ አዛዥ ኮማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ የመንግስትን የሠላም ጥሪ ተቀብሎ ገባ
Mar 30, 2026 101
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰውና ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ሃይል ወታደራዊ አዛዥ ኮማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ ከመንግስት የተደረገለትን የሰላም ጥሪ ተቀብሎ ከነአጃቢዎቹ ላሊበላና አካባቢው ወደ ሚገኘው የመከላከያ ሠራዊት በሰላም ገብቷል። አማራን ነፃ እናወጣለን የሚል መነሻ ይዘን ትግል ብንጀምርም አሁን ላይ ሰከን ብለን ሁኔታውን ስንመለከተው አካሄዳችን የአማራን ህዝብ እና ሀገራችንን ለከፋ አደጋ የሚያጋልጥ ሆኖ ስላገኘነው እና መነሻችንን ስተን የትግል ሂደታችን የከፋ ደረጃ ላይ በመድረሱ የሠላም ጥሪ ተቀብለናል ብሏል። አላማችን በውስጣችን ባሉ አድር ባዮች ፣ በህወሓት እና በውጭ ሀይሎች ተጠልፏል ያለው ኮማንዶ ፍቅሩ እኔ የታሪክ አተላ ተሳታፊ መሆን ስለማልፈልግና የህወሓት ፍላጎት አስፈፃሚ ባለመሆኔ መንግስት ያደረገልኝን የሠላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላማዊ ህይወት ተመልሻለሁ ሲል እውነታውን አስረድቷል። ችግሮች ቢከሰቱም በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፍታት ትክክለኛ አማራጭ መሆን እንዳለበት እምነቱን ገልፆ ባልሰከነ ግንዛቤ ተገፋፍቼ ህዝብን እና ሀገርን መበደሌ ፀፅቶኛል ሲልም ተናግሯል። ከእንግዲህ ካለፈው ስህተት ተምሬ ሀገሬን እና ህዝቤን ለመካስ ዝግጁ በመሆን ወደ ሰላማዊ ትግሉ ተቀላቅያለሁ ያለው ኮማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ ሁሉም በጫካ የሚገኙ አባላት የመንግስትን የሠላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል። በአማራ ክልል የሚሥተዋለውን ግጭት በማሥቀረት ክልሉን ከጦርነት ቀጣና ወደ ልማታዊ እንቅስቃሴ ማሸጋገር እንደሚገባም አንስቷል። የሀገራችንን እና የህዝባችንን ሰላም ማረጋገጥ ጊዜው የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን ያሠመረበት ኮማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ ለኢትዮጵያ የእድገት ማነቆ ሆነው የቀጠሉ ጠላቶቻችንን በጋራ ለመመከት ዝግጁ መሆኑን በአሥተያየቱ አሥረድቷል። ውሳኔው በክልሉ የሚታየውን አለመረጋጋት በውይይትና በድርድር መፍትሄ ለመፈለግ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ይጠበቃል ሲል መረጃውን ያደረሠን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ነው።
ኢትዮጵያ በ11ኛው የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ንቁ ተሳትፎ አድርጋለች-አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን
Mar 30, 2026 275
አዲስ አበባ፤መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተሳተፉበት 11ኛው የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ንቁ ተሳትፎ ማድረጓን በቤንሉክስ አገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ገለጹ። 11ኛው የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ "የተለወጠ እና የታደሰ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት- ተግዳሮት ለበዛባት ዓለም" በሚል መሪ ሀሳብ መጋቢት 19 እና 20 / 2018 ዓ.ም በኢኳቶሪያል ጊኒ ማላቦ ከተማ ተካሂዷል። በጉባኤው ተገኝተው ንግግር ያደርጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያሏቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። ውይይቱን የተከታተሉት በቤንሉክስ ሀገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመድረኩ የድርጅቱን አስፊላጊነት እና ተፅእኖ ፈጣሪነት የሚያሳድጉ ገንቢ ሀሳቦችን ማካፈላቸውን ተናግረዋል። እንደ አምባሳደር እሸቴ ገለጸ፥ ኢትዮጵያ የባለ ብዙ ወገን ግንኙነትን የመደገፍ የቆየ እሴትና መርህ ያለት ሀገር ናት። በዚህም የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅትን ከመሰረቱ ጥቂት ሀገራት አንዷ መሆኗን ጠቁመው፤ ድርጅቱ እንዲጠናከርም የገንዘብ መዋጮዋን በአግባቡ ከመክፈል ጀምሮ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ እያደረገች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ማንኛውም ሀገር ብቻውን ሊሰራ የሚችለው ነገር የለም ያሉት አምባሳደር እሸቴ፤ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር ያላት ተሳትፎ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር በእጅጉ እንደሚያግዛትም ተናግረዋል፡፡ እነዚህን እድሎች በአግባቡ ለመጠቀም ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት ወጣቶቻቸውን በብዙ መልኩ ማዘጋጀት አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት እ.አ.አ በ1975 በጆርጅታውን - ጉውያና የተመሰረተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 79 አባል ሀገራት አሉት።
የሀገረ መንግሥት ግንባታው ምሰሶ የሆኑትን ተቋማት የመገንባትና የማደራጀት ሥራ በልዩ ቁርጠኝነት ተከናውኗል
Mar 30, 2026 197
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦የሀገረ መንግሥት ግንባታው ምሰሶ የሆኑትን ተቋማት የመገንባትና የማደራጀት ሥራ በልዩ ቁርጠኝነት ተከናውኗል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የኢፌድሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አካታች ፖለቲካዊ ለውጦች ለጽኑ ሀገራዊ መሠረት በሚል መግለጫ አውጥቷል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ ጽሁፍ እንደሚከተለው ቀርቧል፦ አካታች ፖለቲካዊ ለውጦች ለጽኑ ሀገራዊ መሠረት የኢፌድሪ መንግሥት ባለፉት የለውጥ ዓመታት አገራችንን ከነበረችበት ስር የሰደደ ፖለቲካዊ ቀውስ አውጥቶ ወደ ተሟላ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማሸጋገር የነደፋቸውን ስልታዊ ግቦች በላቀ ጽናትና ስኬት ወደ ተግባር ቀይሯል። የዚህ ታሪካዊ ሽግግር ዋነኛ ስኬት ለዘመናት ኢትዮጵያን ሲንድ የነበረውን "የመሐል እና የዳር" አግላይ ፖለቲካዊ ትርክት በመስበር እያንዳንዱ ዜጋና እያንዳንዱ አካባቢ የሥልጣንና የሀብት ፍትሃዊ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ኅብረ-ብሔራዊ አንድነት መገንባቱ ነው። ይህ ለውጥ ኢትዮጵያ የጥቂቶች ሳይሆን የሁላችንም የጋራ ቤት መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ መሠረታዊ ድል ነው። ለዘላቂ ሰላምና ለአገራዊ ህልውና መረጋገጥ በትውልዶች መካከል ድልድይ የሚሆን የወል ትርክት ግንባታ ላይ የተመዘገቡት ድሎች የለውጡ መንግሥት ታላቅ ፖለቲካዊ ስኬቶች ሲሆኑ ሃገራችንን ለዘመናት በቅራኔ ውስጥ ዘፍቀው የቆዩ አግላይ ትርክቶች እንዲከስሙ በማድረግ፣ በምትካቸው የሁላችንንም ታሪክና አሻራ የሚዘክሩ የጋራ ትርክቶች በተግባር እንዲጎለብቱ ተደርጓል። በዚህም የታሪክና የማንነት መገለጫ የሆኑት የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የታላቁ ሕዳሴ ግድብና በገበታ ለሸገር፣ ለሀገር እና ለትውልድ መርሐ-ግብር የተገነቡ ግዙፍ የቱሪዝም መዳረሻዎች የጋራ አገራዊ ኩራታችንን ከፍ አድርገውታል። ብዝኃነትን በውበትነት በመቀበል በብሔራዊ ምክክር መድረክ የቀጠለው ትናንትን የማከም ጉዞም ትናንት በጥርጣሬና በክፍፍል ይናጥ የነበረውን አገራዊ ትርክት ቀስበቀስ በተግባር ወደ ተረጋገጠ 'ወንድማማችነትና የጋራ ብልጽግና' እየመራው ይገኛል። የሀገረ መንግሥት ግንባታው ምሰሶ የሆኑትን ተቋማት የመገንባትና የማደራጀት ሥራ በልዩ ቁርጠኝነት ተከናውኗል።በተለይም የፀጥታ፣ የፍትሕና የዴሞክራሲ ተቋማት ለሕዝብና ለሕግ ብቻ ተገዥ እንዲሆኑ የተደረገው ሪፎርም ስር-ነቀል ለውጥ አምጥቷል። በዚህም መሠረት እንደ ምርጫ ቦርድና ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ያሉ የዴሞክራሲ ተቋማት በገለልተኛ አመራር እንዲዋቀሩ መደረጉ፣ የመከላከያና የደኅንነት ተቋማት ከአገራዊ ተልእኮ ውጭ ከማንኛውም የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እንዲጸዱ መደረጋቸውና የፍትሕ ሥርዓቱ በነጻነት እንዲሠራ የተዘረጋው አሠራር የተቋማዊ ሪፎርማችን ሕያው ማሳያዎች ናቸው። ይህ ስር-ነቀል የፖለቲካ ለውጥ በውስጥ መረጋጋትና በአገራዊ መግባባት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ኢትዮጵያ የነበሩባትን የህልውና ሥጋቶች በጽናት እንድትወጣ አስችሏታል። ሉዓላዊነታችንን በፖለቲካዊ ብስለትና በአመራር ጥንካሬ የማስከበር አቅማችን መጎልበቱ፣ የመንግሥትን የፖሊሲ ማስፈጸም ብቃት ከማሳየቱም በላይ አገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ አሸጋግሯታል። እነዚህ የፖለቲካ ድሎች በውስጥ የታየው አንጻራዊ የሰላም መስፈን፣ የፖለቲካ ምሕዳሩ መስፋትና የተቋማት መጠናከር ቀጥተኛ ውጤቶች በመሆናቸው አገራችን ለምታደርገው የብልጽግና ጉዞ መሰረት እየጣሉ ይገኛል። በአጠቃላይ እነዚህ የፖለቲካ ትልሞችና የተጨበጡ ፍሬዎች ኢትዮጵያን ወደ አዲስና የተሻለ የዴሞክራሲ ልምምድ አሸጋግረዋታል። የተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎ ማደግ፣ የመንግሥት ተቀባይነት በሕዝብ ዘንድ ጎልቶ መታየትና የሪፎርም ሥራዎች ስኬታማነት ለብልጽግና ጉዟችን አስተማማኝ ዋስትናዎች እየሆኑ መጥተዋል። መንግሥት ይህንኑ የዴሞክራሲና የብልጽግና ጎዳና አጠናክሮ በመቀጠል፣ ለትውልድ የምትመች፣ የበለጸገችና ሉዓላዊነቷ የተከበረች ኢትዮጵያን የመገንባት ታሪካዊ ኃላፊነቱን በላቀ ቁርጠኝነት መወጣቱን ይቀጥላል። መጋቢት 21/2018 ዓ.ም የኢፌድሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ሕዝቡን ያሳተፉ የፀጥታ ማስከበር ሥራ እየተከናወነ ነው
Mar 29, 2026 589
ገንዳውኃ፤ መጋቢት20/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን ሕዝቡን ያሳተፉ የፀጥታ ማስከበር ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለጸ። በዞኑ በወቅታዊ የሰላምና ልማት ተግባራት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በገንዳ ውኃ ከተማ ተካሂዷል። የአማራ ክልል የአካባቢና ደን ጥበቃ ባለሥልጣን ምክትል ኃላፊ ተሾመ አግማስ በዚሁ ወቅት፤ በዞኑ አስተማማኝ ሰላምን በማስፈን የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ የልማትና የፀጥታ ሥራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል። ከሰላም ማስፈን ሥራ ጎን ለጎን የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ፈጥኖ ለመጨረስና አዳዲስ የልማት ሥራዎችን ለማስጀመር የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉንም አንስተዋል። ሕዝቡ የልማት ሥራዎችን ከጸጥታ ማስከበር ተግባር ጋር በማጣመር ለማስኬድ እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶች እንዲጠናከሩም ጠቀዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አሥተዳዳሪ እያሱ ይላቅ በበኩላቸው፤ በእያንዳንዱ ተግባር የሕዝቡን ተሳትፎ በማረጋገጥ የሰላሙና የልማቱ ባለቤት ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን አረጋግጠዋል። ይህን ተከትሎም በዞኑ ያለው ሰላም እየተሻሻለ መምጣቱንና ኅብረተሰቡን በማሳተፍ እየተከናወነ ያለው የሕግ ማስከበር ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።
እስካሁን ከ28 ሚሊየን በላይ መራጮች የምርጫ ካርድ ወስደዋል
Mar 28, 2026 676
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018 (ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከ28 ሚሊየን በላይ መራጮች የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ምርጫ ቦርድ እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 28 ሚሊዮን 365 ሺህ 310 መራጮች መመዝገባቸውን አስታውቋል። ከነዚህም 15 ሚሊዮን 317 ሺህ 567 ወንዶች እና 13 ሚሊዮን 47 ሺህ 743 ሴቶች ናቸው። በተያያዘም ቦርዱ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ እንዲያደርጉባቸው የተመደቡ የሕዝብ እና የንግድ መገናኛ ብዙኃን ብዛትን ይፋ አድርጓል። ጠቅላላ የመገናኛ ብዙኃን ብዛት 50 ሲሆን ሬዲዮ 24፣ ቴሌቪዥን 20 ጋዜጦች 6 መሆናቸውን ቦርዱ አመልክቷል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዳበረ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የምንከፍትበት ነው
Mar 28, 2026 665
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ፉክክር በማድረግ ለዳበረ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የምንከፍትበት መድረክ ነው ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ይገኛል። የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አማራጭ ሃሳቦችን ለህዝብ በማቅረብ ድምፅ ማግኘት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እያደረጉ ነው። በሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫም ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ፉክክር በማድረግ ለኢትዮጵያ የዳበረ የመድበለ ፓርቲ ባህል ግንባታ እንደሚጠቀሙበት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) ዋና ጸኃፊ ዋሲሁን ተስፋዬ፤ የኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ የልምምድ ዕድል እንዳለው ተናግረዋል። ይህም ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ፉክክር በማድረግ የዳበረ የመድበለ ፓርቲ ምኅዳር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ገንቢ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አንስተዋል። ለአብነትም የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) በራሱ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤውን በማካሄድ ዴሞክራሲያዊ የአመራር ለውጥ ማድረጉን አስረድተዋል። የፖርቲው ውስጠ-ዴሞክራሲም የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ለማጠናከር ጉልህ ድርሻ እንዳለው አንስተዋል። የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሕብረት(ኢዴሕ) ሊቀመንበር ገብሩ በርሔ፤ መንግስት ሰፊ የፖለቲካ ምኅዳር እንዲፈጠር በማድረግ አስደናቂ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም የፓርቲዎችን ሚዛናዊነት ማስጠበቅ የሚያስችል ምቹ የድጋፍና ክትትል ሥርዓት መፍጠሩን ገልጸዋል። ፓርቲያቸውም የኢትዮጵያን ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ፉክክር ባህል በማጎልበት ለመድበለ ፓርቲ ግንባታ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ አንተዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሐዊና ገለልተኛ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስቻይ ሁኔታ ፈጥሮ እየሰራ ነው ያሉት ደግሞ የአገው ብሄራዊ ሸንጎ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍትሕዓለው ዓባይ ናቸው። በዚህም ሰላም ለኢትዮጵያ የፓርቲዎች ጥምረት በሕዝብ ተወካዮችና በክልል ምክር ቤቶች የሚወከሉ ዕጩዎችን በማቅረብ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ የፉክክር ሂደትም አማራጭ የፖሊሲ ሀሳባቸውን በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ለህዝብ በማቅረብ ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ ተናግረዋል። በህዝብ ይሁንታ የተመሰረተ መንግስት በማቋቋም ጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ለመገንባት ዜጎች በምርጫ ሂደት የሚሰጡት ድምፅ ከፍተኛ ዋጋ እንዳለውም ጠቁመዋል። ለዚህም የፓርቲዎቻቸውን አመራር፣ አባላትና ደጋፊዎች የምርጫን ዋጋ በማስገንዘብ የዴሞክራሲ ባህልን ለማጎልበት በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆኑን አረጋግጠዋል። መራጩ ህዝብም የምርጫ ካርድ በማውጣት ይበጀኛል ለሚለው ፓርቲ ድምፅ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት ማድረግ እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚመደብላቸውን ነፃ የአየር ሰዓት በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል
Mar 28, 2026 516
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚመደብላቸውን ነፃ የአየር ሰዓት በመጠቀም ፕሮግራሞቻቸውን በአግባቡ ማስተዋወቅ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስገነዘበ። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የአየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዚሁ ወቅት፤ ቦርዱ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከሚያደርጋቸው ዝግጅቶች መካከል አንዱ ለፓርቲዎች ነፃ የአየር ሰዓት ድልድል ማድረግ ነው ብለዋል። ይህ የነፃ የአየር ሰዓት ድልድል የሚካሄደውም ቦርዱ ከመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ጋር በመሆን ባበለጸገው አዲስ ሲስተም መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ አሰራር የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን ሀሳብ፣ ፖሊሲ እና ፕሮግራም ለመራጩ ህዝብ እንዲያስተዋውቁ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰው፤ ፓርቲዎች የሚመደብላቸውን ነፃ የአየር ሰዓት በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል። በተለይም ፓርቲዎቹ ባስመዘገቧቸው ሴት እና አካል ጉዳተኛ ዕጩዎች ብዛት ልክ ተጨማሪ ነፃ የአየር ሰዓት የሚፈቅድ አዋጅ በመፅደቁ፤ አሰራሩ በዚህ ምርጫ ተግባራዊ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀይማኖት ዘለቀ በበኩላቸው፤ ነፃ የአየር ሰዓቱ መራጩ ህዝብ ድምፅ በሚሰጥበት ወቅት በዕውቀት ላይ ተመስርቶ እንዲወስን ያስችላል ብለዋል። ነፃ የአየር ሰዓቱ ለ47 የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች በዕጣ ድልድል እንደሚደረግ ተናግረዋል። የዘንድሮው ድልድል ከ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጋር ሲነጻጸር የ10 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቁመው፤ ይህም በ50 መገናኛ ብዙሃን (በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን እና በጋዜጣ) የሚስተናገድ ይሆናልም ብለዋል። ይህ ድልድል ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ትልቅ አስተዋፅኦ ስላለው፣ ፓርቲዎች የአየር ሰዓቱን በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙ አስገንዝበዋል። መገናኛ ብዙሃንም ለፓርቲዎቹ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የአየር ሰዓት አጠቃቀም ቅዳሜ፣ እሁድ እና የበዓላት ቀናትን ሳይጨምር ከመጋቢት 23 እስከ ግንቦት19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተፈፃሚ እንደሚሆን ተገልጿል።
በምርጫው በንቃት በመሳተፍ የሚወክለንን ለመምረጥ ካርድ እየወሰድን ነው
Mar 28, 2026 434
ቡታጅራ ፤መጋቢት 19/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ የሚወክለንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ እየወሰድን ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የቡታጅራ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፣ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድ ሲሆን፤ ለዚሁ ተግባር የሚያስፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። ከእነዚህ ዝግጅቶች መካከል ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ እየወሰዱ ይገኛሉ። ኢዜአ በቡታጅራ ከተማ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ በቀጣዩ ምርጫ ለመሳተፍና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ይገኛሉ። በከተማዋ የእርንዛፍ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ባህርነሽ መሀመድ፤ "የመራጭነት ካርድ በመውሰድ የሚጠቅመኝን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ" ብለዋል። የምርጫ ካርድ መያዝ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም እንዲችሉ ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ፣ ሁሉም የምርጫ ካርድ መያዝ እንዳለበትም ይመክራሉ። ሌላኛው የከተማዋ የ02 ቀበሌ ነዋሪ አቶ ቢራቱ ጠረጋ በበኩላቸው፤ የሕዝብን የልማት ፍላጎትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፓርቲ ለመለየት የምርጫ ክርክሮችን በንቃት እየተከታተሉ መሆኑን ጠቁመዋል። የአካል ጉዳተኛ የሆኑት አቶ ቢራቱ፤ በምርጫው አካል ጉዳተኞችን በትምህርትና በሥራ እድል ተሳታፊ እና ተጠቃሚ የሚያደርግ ፓርቲ እንደሚመርጡ ተናግረዋል። በከተማዋ የ04 ሸባብ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ከድጃ ሳሉሲን እና የ03 ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሪት መለሰች ተካም እንዲሁ፤ የሕዝቡን የልማት ጥያቄ የሚመልስ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። የካርድ አሰጣጥ ሂደቱም ምቹ እና ቀልጣፋ መሆኑን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል 1 አስፈጻሚ አቶ እስጢፋኖስ ፍቃዱ፤ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መራጮች እየተመዘገቡ መሆኑን አረጋግጠዋል። በምርጫ ክልሉ በሚገኙ 87 የምርጫ ጣቢያዎች በሙሉ በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ሂደት በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።
ፖለቲካ
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ሃይል ወታደራዊ አዛዥ ኮማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ የመንግስትን የሠላም ጥሪ ተቀብሎ ገባ
Mar 30, 2026 101
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰውና ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ሃይል ወታደራዊ አዛዥ ኮማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ ከመንግስት የተደረገለትን የሰላም ጥሪ ተቀብሎ ከነአጃቢዎቹ ላሊበላና አካባቢው ወደ ሚገኘው የመከላከያ ሠራዊት በሰላም ገብቷል። አማራን ነፃ እናወጣለን የሚል መነሻ ይዘን ትግል ብንጀምርም አሁን ላይ ሰከን ብለን ሁኔታውን ስንመለከተው አካሄዳችን የአማራን ህዝብ እና ሀገራችንን ለከፋ አደጋ የሚያጋልጥ ሆኖ ስላገኘነው እና መነሻችንን ስተን የትግል ሂደታችን የከፋ ደረጃ ላይ በመድረሱ የሠላም ጥሪ ተቀብለናል ብሏል። አላማችን በውስጣችን ባሉ አድር ባዮች ፣ በህወሓት እና በውጭ ሀይሎች ተጠልፏል ያለው ኮማንዶ ፍቅሩ እኔ የታሪክ አተላ ተሳታፊ መሆን ስለማልፈልግና የህወሓት ፍላጎት አስፈፃሚ ባለመሆኔ መንግስት ያደረገልኝን የሠላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላማዊ ህይወት ተመልሻለሁ ሲል እውነታውን አስረድቷል። ችግሮች ቢከሰቱም በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፍታት ትክክለኛ አማራጭ መሆን እንዳለበት እምነቱን ገልፆ ባልሰከነ ግንዛቤ ተገፋፍቼ ህዝብን እና ሀገርን መበደሌ ፀፅቶኛል ሲልም ተናግሯል። ከእንግዲህ ካለፈው ስህተት ተምሬ ሀገሬን እና ህዝቤን ለመካስ ዝግጁ በመሆን ወደ ሰላማዊ ትግሉ ተቀላቅያለሁ ያለው ኮማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ ሁሉም በጫካ የሚገኙ አባላት የመንግስትን የሠላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል። በአማራ ክልል የሚሥተዋለውን ግጭት በማሥቀረት ክልሉን ከጦርነት ቀጣና ወደ ልማታዊ እንቅስቃሴ ማሸጋገር እንደሚገባም አንስቷል። የሀገራችንን እና የህዝባችንን ሰላም ማረጋገጥ ጊዜው የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን ያሠመረበት ኮማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ ለኢትዮጵያ የእድገት ማነቆ ሆነው የቀጠሉ ጠላቶቻችንን በጋራ ለመመከት ዝግጁ መሆኑን በአሥተያየቱ አሥረድቷል። ውሳኔው በክልሉ የሚታየውን አለመረጋጋት በውይይትና በድርድር መፍትሄ ለመፈለግ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ይጠበቃል ሲል መረጃውን ያደረሠን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ነው።
ኢትዮጵያ በ11ኛው የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ንቁ ተሳትፎ አድርጋለች-አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን
Mar 30, 2026 275
አዲስ አበባ፤መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተሳተፉበት 11ኛው የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ንቁ ተሳትፎ ማድረጓን በቤንሉክስ አገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ገለጹ። 11ኛው የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ "የተለወጠ እና የታደሰ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት- ተግዳሮት ለበዛባት ዓለም" በሚል መሪ ሀሳብ መጋቢት 19 እና 20 / 2018 ዓ.ም በኢኳቶሪያል ጊኒ ማላቦ ከተማ ተካሂዷል። በጉባኤው ተገኝተው ንግግር ያደርጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያሏቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። ውይይቱን የተከታተሉት በቤንሉክስ ሀገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመድረኩ የድርጅቱን አስፊላጊነት እና ተፅእኖ ፈጣሪነት የሚያሳድጉ ገንቢ ሀሳቦችን ማካፈላቸውን ተናግረዋል። እንደ አምባሳደር እሸቴ ገለጸ፥ ኢትዮጵያ የባለ ብዙ ወገን ግንኙነትን የመደገፍ የቆየ እሴትና መርህ ያለት ሀገር ናት። በዚህም የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅትን ከመሰረቱ ጥቂት ሀገራት አንዷ መሆኗን ጠቁመው፤ ድርጅቱ እንዲጠናከርም የገንዘብ መዋጮዋን በአግባቡ ከመክፈል ጀምሮ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ እያደረገች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ማንኛውም ሀገር ብቻውን ሊሰራ የሚችለው ነገር የለም ያሉት አምባሳደር እሸቴ፤ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር ያላት ተሳትፎ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር በእጅጉ እንደሚያግዛትም ተናግረዋል፡፡ እነዚህን እድሎች በአግባቡ ለመጠቀም ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት ወጣቶቻቸውን በብዙ መልኩ ማዘጋጀት አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ፣ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት እ.አ.አ በ1975 በጆርጅታውን - ጉውያና የተመሰረተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 79 አባል ሀገራት አሉት።
የሀገረ መንግሥት ግንባታው ምሰሶ የሆኑትን ተቋማት የመገንባትና የማደራጀት ሥራ በልዩ ቁርጠኝነት ተከናውኗል
Mar 30, 2026 197
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦የሀገረ መንግሥት ግንባታው ምሰሶ የሆኑትን ተቋማት የመገንባትና የማደራጀት ሥራ በልዩ ቁርጠኝነት ተከናውኗል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የኢፌድሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አካታች ፖለቲካዊ ለውጦች ለጽኑ ሀገራዊ መሠረት በሚል መግለጫ አውጥቷል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ ጽሁፍ እንደሚከተለው ቀርቧል፦ አካታች ፖለቲካዊ ለውጦች ለጽኑ ሀገራዊ መሠረት የኢፌድሪ መንግሥት ባለፉት የለውጥ ዓመታት አገራችንን ከነበረችበት ስር የሰደደ ፖለቲካዊ ቀውስ አውጥቶ ወደ ተሟላ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማሸጋገር የነደፋቸውን ስልታዊ ግቦች በላቀ ጽናትና ስኬት ወደ ተግባር ቀይሯል። የዚህ ታሪካዊ ሽግግር ዋነኛ ስኬት ለዘመናት ኢትዮጵያን ሲንድ የነበረውን "የመሐል እና የዳር" አግላይ ፖለቲካዊ ትርክት በመስበር እያንዳንዱ ዜጋና እያንዳንዱ አካባቢ የሥልጣንና የሀብት ፍትሃዊ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ኅብረ-ብሔራዊ አንድነት መገንባቱ ነው። ይህ ለውጥ ኢትዮጵያ የጥቂቶች ሳይሆን የሁላችንም የጋራ ቤት መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ መሠረታዊ ድል ነው። ለዘላቂ ሰላምና ለአገራዊ ህልውና መረጋገጥ በትውልዶች መካከል ድልድይ የሚሆን የወል ትርክት ግንባታ ላይ የተመዘገቡት ድሎች የለውጡ መንግሥት ታላቅ ፖለቲካዊ ስኬቶች ሲሆኑ ሃገራችንን ለዘመናት በቅራኔ ውስጥ ዘፍቀው የቆዩ አግላይ ትርክቶች እንዲከስሙ በማድረግ፣ በምትካቸው የሁላችንንም ታሪክና አሻራ የሚዘክሩ የጋራ ትርክቶች በተግባር እንዲጎለብቱ ተደርጓል። በዚህም የታሪክና የማንነት መገለጫ የሆኑት የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የታላቁ ሕዳሴ ግድብና በገበታ ለሸገር፣ ለሀገር እና ለትውልድ መርሐ-ግብር የተገነቡ ግዙፍ የቱሪዝም መዳረሻዎች የጋራ አገራዊ ኩራታችንን ከፍ አድርገውታል። ብዝኃነትን በውበትነት በመቀበል በብሔራዊ ምክክር መድረክ የቀጠለው ትናንትን የማከም ጉዞም ትናንት በጥርጣሬና በክፍፍል ይናጥ የነበረውን አገራዊ ትርክት ቀስበቀስ በተግባር ወደ ተረጋገጠ 'ወንድማማችነትና የጋራ ብልጽግና' እየመራው ይገኛል። የሀገረ መንግሥት ግንባታው ምሰሶ የሆኑትን ተቋማት የመገንባትና የማደራጀት ሥራ በልዩ ቁርጠኝነት ተከናውኗል።በተለይም የፀጥታ፣ የፍትሕና የዴሞክራሲ ተቋማት ለሕዝብና ለሕግ ብቻ ተገዥ እንዲሆኑ የተደረገው ሪፎርም ስር-ነቀል ለውጥ አምጥቷል። በዚህም መሠረት እንደ ምርጫ ቦርድና ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ያሉ የዴሞክራሲ ተቋማት በገለልተኛ አመራር እንዲዋቀሩ መደረጉ፣ የመከላከያና የደኅንነት ተቋማት ከአገራዊ ተልእኮ ውጭ ከማንኛውም የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እንዲጸዱ መደረጋቸውና የፍትሕ ሥርዓቱ በነጻነት እንዲሠራ የተዘረጋው አሠራር የተቋማዊ ሪፎርማችን ሕያው ማሳያዎች ናቸው። ይህ ስር-ነቀል የፖለቲካ ለውጥ በውስጥ መረጋጋትና በአገራዊ መግባባት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ኢትዮጵያ የነበሩባትን የህልውና ሥጋቶች በጽናት እንድትወጣ አስችሏታል። ሉዓላዊነታችንን በፖለቲካዊ ብስለትና በአመራር ጥንካሬ የማስከበር አቅማችን መጎልበቱ፣ የመንግሥትን የፖሊሲ ማስፈጸም ብቃት ከማሳየቱም በላይ አገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ አሸጋግሯታል። እነዚህ የፖለቲካ ድሎች በውስጥ የታየው አንጻራዊ የሰላም መስፈን፣ የፖለቲካ ምሕዳሩ መስፋትና የተቋማት መጠናከር ቀጥተኛ ውጤቶች በመሆናቸው አገራችን ለምታደርገው የብልጽግና ጉዞ መሰረት እየጣሉ ይገኛል። በአጠቃላይ እነዚህ የፖለቲካ ትልሞችና የተጨበጡ ፍሬዎች ኢትዮጵያን ወደ አዲስና የተሻለ የዴሞክራሲ ልምምድ አሸጋግረዋታል። የተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎ ማደግ፣ የመንግሥት ተቀባይነት በሕዝብ ዘንድ ጎልቶ መታየትና የሪፎርም ሥራዎች ስኬታማነት ለብልጽግና ጉዟችን አስተማማኝ ዋስትናዎች እየሆኑ መጥተዋል። መንግሥት ይህንኑ የዴሞክራሲና የብልጽግና ጎዳና አጠናክሮ በመቀጠል፣ ለትውልድ የምትመች፣ የበለጸገችና ሉዓላዊነቷ የተከበረች ኢትዮጵያን የመገንባት ታሪካዊ ኃላፊነቱን በላቀ ቁርጠኝነት መወጣቱን ይቀጥላል። መጋቢት 21/2018 ዓ.ም የኢፌድሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ሕዝቡን ያሳተፉ የፀጥታ ማስከበር ሥራ እየተከናወነ ነው
Mar 29, 2026 589
ገንዳውኃ፤ መጋቢት20/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን ሕዝቡን ያሳተፉ የፀጥታ ማስከበር ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለጸ። በዞኑ በወቅታዊ የሰላምና ልማት ተግባራት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በገንዳ ውኃ ከተማ ተካሂዷል። የአማራ ክልል የአካባቢና ደን ጥበቃ ባለሥልጣን ምክትል ኃላፊ ተሾመ አግማስ በዚሁ ወቅት፤ በዞኑ አስተማማኝ ሰላምን በማስፈን የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ የልማትና የፀጥታ ሥራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል። ከሰላም ማስፈን ሥራ ጎን ለጎን የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ፈጥኖ ለመጨረስና አዳዲስ የልማት ሥራዎችን ለማስጀመር የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉንም አንስተዋል። ሕዝቡ የልማት ሥራዎችን ከጸጥታ ማስከበር ተግባር ጋር በማጣመር ለማስኬድ እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶች እንዲጠናከሩም ጠቀዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አሥተዳዳሪ እያሱ ይላቅ በበኩላቸው፤ በእያንዳንዱ ተግባር የሕዝቡን ተሳትፎ በማረጋገጥ የሰላሙና የልማቱ ባለቤት ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን አረጋግጠዋል። ይህን ተከትሎም በዞኑ ያለው ሰላም እየተሻሻለ መምጣቱንና ኅብረተሰቡን በማሳተፍ እየተከናወነ ያለው የሕግ ማስከበር ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።
እስካሁን ከ28 ሚሊየን በላይ መራጮች የምርጫ ካርድ ወስደዋል
Mar 28, 2026 676
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018 (ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከ28 ሚሊየን በላይ መራጮች የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ምርጫ ቦርድ እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 28 ሚሊዮን 365 ሺህ 310 መራጮች መመዝገባቸውን አስታውቋል። ከነዚህም 15 ሚሊዮን 317 ሺህ 567 ወንዶች እና 13 ሚሊዮን 47 ሺህ 743 ሴቶች ናቸው። በተያያዘም ቦርዱ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ እንዲያደርጉባቸው የተመደቡ የሕዝብ እና የንግድ መገናኛ ብዙኃን ብዛትን ይፋ አድርጓል። ጠቅላላ የመገናኛ ብዙኃን ብዛት 50 ሲሆን ሬዲዮ 24፣ ቴሌቪዥን 20 ጋዜጦች 6 መሆናቸውን ቦርዱ አመልክቷል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዳበረ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የምንከፍትበት ነው
Mar 28, 2026 665
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ፉክክር በማድረግ ለዳበረ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የምንከፍትበት መድረክ ነው ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ይገኛል። የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አማራጭ ሃሳቦችን ለህዝብ በማቅረብ ድምፅ ማግኘት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እያደረጉ ነው። በሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫም ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ፉክክር በማድረግ ለኢትዮጵያ የዳበረ የመድበለ ፓርቲ ባህል ግንባታ እንደሚጠቀሙበት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) ዋና ጸኃፊ ዋሲሁን ተስፋዬ፤ የኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ የልምምድ ዕድል እንዳለው ተናግረዋል። ይህም ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ፉክክር በማድረግ የዳበረ የመድበለ ፓርቲ ምኅዳር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ገንቢ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አንስተዋል። ለአብነትም የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) በራሱ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤውን በማካሄድ ዴሞክራሲያዊ የአመራር ለውጥ ማድረጉን አስረድተዋል። የፖርቲው ውስጠ-ዴሞክራሲም የሀገርን የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ለማጠናከር ጉልህ ድርሻ እንዳለው አንስተዋል። የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሕብረት(ኢዴሕ) ሊቀመንበር ገብሩ በርሔ፤ መንግስት ሰፊ የፖለቲካ ምኅዳር እንዲፈጠር በማድረግ አስደናቂ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም የፓርቲዎችን ሚዛናዊነት ማስጠበቅ የሚያስችል ምቹ የድጋፍና ክትትል ሥርዓት መፍጠሩን ገልጸዋል። ፓርቲያቸውም የኢትዮጵያን ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ፉክክር ባህል በማጎልበት ለመድበለ ፓርቲ ግንባታ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ አንተዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሐዊና ገለልተኛ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስቻይ ሁኔታ ፈጥሮ እየሰራ ነው ያሉት ደግሞ የአገው ብሄራዊ ሸንጎ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍትሕዓለው ዓባይ ናቸው። በዚህም ሰላም ለኢትዮጵያ የፓርቲዎች ጥምረት በሕዝብ ተወካዮችና በክልል ምክር ቤቶች የሚወከሉ ዕጩዎችን በማቅረብ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ የፉክክር ሂደትም አማራጭ የፖሊሲ ሀሳባቸውን በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ለህዝብ በማቅረብ ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ ተናግረዋል። በህዝብ ይሁንታ የተመሰረተ መንግስት በማቋቋም ጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ለመገንባት ዜጎች በምርጫ ሂደት የሚሰጡት ድምፅ ከፍተኛ ዋጋ እንዳለውም ጠቁመዋል። ለዚህም የፓርቲዎቻቸውን አመራር፣ አባላትና ደጋፊዎች የምርጫን ዋጋ በማስገንዘብ የዴሞክራሲ ባህልን ለማጎልበት በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆኑን አረጋግጠዋል። መራጩ ህዝብም የምርጫ ካርድ በማውጣት ይበጀኛል ለሚለው ፓርቲ ድምፅ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት ማድረግ እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚመደብላቸውን ነፃ የአየር ሰዓት በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል
Mar 28, 2026 516
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚመደብላቸውን ነፃ የአየር ሰዓት በመጠቀም ፕሮግራሞቻቸውን በአግባቡ ማስተዋወቅ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስገነዘበ። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የአየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዚሁ ወቅት፤ ቦርዱ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከሚያደርጋቸው ዝግጅቶች መካከል አንዱ ለፓርቲዎች ነፃ የአየር ሰዓት ድልድል ማድረግ ነው ብለዋል። ይህ የነፃ የአየር ሰዓት ድልድል የሚካሄደውም ቦርዱ ከመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ጋር በመሆን ባበለጸገው አዲስ ሲስተም መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ አሰራር የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን ሀሳብ፣ ፖሊሲ እና ፕሮግራም ለመራጩ ህዝብ እንዲያስተዋውቁ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰው፤ ፓርቲዎች የሚመደብላቸውን ነፃ የአየር ሰዓት በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል። በተለይም ፓርቲዎቹ ባስመዘገቧቸው ሴት እና አካል ጉዳተኛ ዕጩዎች ብዛት ልክ ተጨማሪ ነፃ የአየር ሰዓት የሚፈቅድ አዋጅ በመፅደቁ፤ አሰራሩ በዚህ ምርጫ ተግባራዊ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀይማኖት ዘለቀ በበኩላቸው፤ ነፃ የአየር ሰዓቱ መራጩ ህዝብ ድምፅ በሚሰጥበት ወቅት በዕውቀት ላይ ተመስርቶ እንዲወስን ያስችላል ብለዋል። ነፃ የአየር ሰዓቱ ለ47 የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች በዕጣ ድልድል እንደሚደረግ ተናግረዋል። የዘንድሮው ድልድል ከ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጋር ሲነጻጸር የ10 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቁመው፤ ይህም በ50 መገናኛ ብዙሃን (በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን እና በጋዜጣ) የሚስተናገድ ይሆናልም ብለዋል። ይህ ድልድል ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ትልቅ አስተዋፅኦ ስላለው፣ ፓርቲዎች የአየር ሰዓቱን በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙ አስገንዝበዋል። መገናኛ ብዙሃንም ለፓርቲዎቹ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የአየር ሰዓት አጠቃቀም ቅዳሜ፣ እሁድ እና የበዓላት ቀናትን ሳይጨምር ከመጋቢት 23 እስከ ግንቦት19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተፈፃሚ እንደሚሆን ተገልጿል።
በምርጫው በንቃት በመሳተፍ የሚወክለንን ለመምረጥ ካርድ እየወሰድን ነው
Mar 28, 2026 434
ቡታጅራ ፤መጋቢት 19/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ የሚወክለንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ እየወሰድን ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የቡታጅራ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፣ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድ ሲሆን፤ ለዚሁ ተግባር የሚያስፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። ከእነዚህ ዝግጅቶች መካከል ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ እየወሰዱ ይገኛሉ። ኢዜአ በቡታጅራ ከተማ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ በቀጣዩ ምርጫ ለመሳተፍና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ይገኛሉ። በከተማዋ የእርንዛፍ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ባህርነሽ መሀመድ፤ "የመራጭነት ካርድ በመውሰድ የሚጠቅመኝን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ" ብለዋል። የምርጫ ካርድ መያዝ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም እንዲችሉ ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ፣ ሁሉም የምርጫ ካርድ መያዝ እንዳለበትም ይመክራሉ። ሌላኛው የከተማዋ የ02 ቀበሌ ነዋሪ አቶ ቢራቱ ጠረጋ በበኩላቸው፤ የሕዝብን የልማት ፍላጎትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፓርቲ ለመለየት የምርጫ ክርክሮችን በንቃት እየተከታተሉ መሆኑን ጠቁመዋል። የአካል ጉዳተኛ የሆኑት አቶ ቢራቱ፤ በምርጫው አካል ጉዳተኞችን በትምህርትና በሥራ እድል ተሳታፊ እና ተጠቃሚ የሚያደርግ ፓርቲ እንደሚመርጡ ተናግረዋል። በከተማዋ የ04 ሸባብ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ከድጃ ሳሉሲን እና የ03 ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሪት መለሰች ተካም እንዲሁ፤ የሕዝቡን የልማት ጥያቄ የሚመልስ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። የካርድ አሰጣጥ ሂደቱም ምቹ እና ቀልጣፋ መሆኑን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል 1 አስፈጻሚ አቶ እስጢፋኖስ ፍቃዱ፤ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መራጮች እየተመዘገቡ መሆኑን አረጋግጠዋል። በምርጫ ክልሉ በሚገኙ 87 የምርጫ ጣቢያዎች በሙሉ በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ሂደት በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።
ማህበራዊ
በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ በእናቶች ላይ የሚከሰት የጤና እክልን ለመከላከል ትኩረት ተደርጓል
Mar 30, 2026 29
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ በእናቶች ላይ የሚከሰትን የጤና እክል ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። የጤና ሚኒስቴር በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ ከሚከሰቱ ጤና ችግሮች መካከል አንዱ የሆነው የአዕምሮ ጤና እክል የሚያጋጥማቸውን እናቶች ጤና መጠበቅ ላይ ትኩረት ያደረገ አውደ ጥናት አካሂዷል። በቤልጂየም ትሮፒካል ሜዲሲን ኢኒስቲትዩት፣ በአዲስ አበባና ጎንደር ዩኒቨርስቲዎች ትብብር የተዘጋጀው አውደ ጥናትም የአዕምሮ ጤና እክል የሚጋጥማቸውን እናቶች የጤና ደረጃና የመፍትሔ እርምጃዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በጤና ሚኒስቴር የፖሊሲ፣ ስትራቴጂና ምርምር መሪ ሥራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር አስቴር ጸጋዬ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ የእናቶችና ህጻነትን ሞት ለመቀነስ የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል። እናቶች በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ የሚያጋጥማቸው የአዕምሮ ጤና እክልም ትኩረት የሚፈልግ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል። በእርግዝና ወቅትና ከወሊድ በኋላ ለሚከሰት የአዕምሮ ጤና እክል ተጋላጭነትን ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ለዚህም የባለድርሻ አካላት፣ ከፍተኛ የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ተቋማት ቅንጅት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። በጤና ሚኒስቴር ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችና የአዕምሮ ጤና ዴስክ ኃላፊ ዶክተር ሰላማዊት አየለ፤ በእርግዝናና ከወሊድ በኋላ ከቀላል እስከ ከባድ የሚደርስ የአዕምሮ ጤና እክል የሚያጋጥማቸው እናቶችን በተመለከተ በማህበረሰቡ ዘንድ በተሳሳተ ግንዛቤ ችግሩን ተፈጥሯዊ አድርጎ ይወሰዳል። ይህም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተጋላጭነታቸውን እንደሚያባብስ አስረድተው፤ ለዚህም በጤና ባለሙያዎች የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በቤልጂየም ትሮፒካል ሜዲሲን ኢኒስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር አንተነህ አሰፋ እንደገለጹት፤ የእናቶችን በእርግዝናና ከወሊድ በኋላ የጤና ችግሩን ለመቀነስ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በዘርፉ የመጡ ውጤቶችን በማስቀጠል የጥናትና ምርምር እንዲሁም የዲጂታል ቴክኖሎጂ የትብብር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ የፍትህ ስርዓቷን በዓለም አቀፍ አጋርነት ለማዘመን ቁርጠኛ ናት
Mar 30, 2026 28
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የፍትህ ስርዓቷን ጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት በመፍጠር ለማዘመን በቁርጠኝነት ትሰራለች። በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዓለምአንተ አግደው የተመራ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልዑክ በኔዘርላንድስ ሄግ ስትራቴጂካዊ የስራ ጉብኝት እያደረገ ነው። ልኡኩ ከፍተኛ እውቅና ካላቸው ዓለም አቀፍ የህግ ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያካሄደ ይገኛል። ልዑኩ ከዓለም አቀፉ ቋሚ የግልግል ዳኝነት ፍርድ ቤት (Permanent Court of Arbitration) እና ከሄግ ዓለም አቀፍ የሕግ አካዳሚ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋርም ተወያይቷል። የውይይቶቹ ዋነኛ ትኩረትም በኢትዮጵያ በተለይም በአማራ ክልል እየተከናወነ ለሚገኘው የፍትህ ዘርፍ ማሻሻያ ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከርና ቴክኒካዊ ድጋፎችን ማግኘት እንደሆነ ተመላክቷል። ጉብኝቱ ኢትዮጵያን በቀጣናው የግልግል ዳኝነት ማዕከል የማድረግ አካል ሲሆን በአማራ ክልል ዘመናዊ እና ማዕከላዊ የፍትህ ተቋምን የመገንባት እቅድ ተሞክሮ የመውሰድ ውጥንም ያለው ነው። ከፍተኛ ባለስልጣናቱ በውይይቶቹ ላይ ኢትዮጵያ በጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት የሕግ እና ዳኝነት ስርዓቷን ለማዘመን ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸዋል። በተጨማሪም ልዑኩ በሄግ የሚገኘውን ታሪካዊ የሰላም ቤተ መንግስት (historic Peace Palace) የጎበኙ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያ የፍትህ ዘርፍ የማሻሻያ ጉዞ አስመልክቶ ልምድ የተቀሰመበት እንደሆነም ተመላክቷል። ጉብኝቱ ኢትዮጵያ ያላትን ዓለም አቀፍ የሕግ ትስስር እና የፍትህ ዘርፍ ሪፎርሙን ወደፊት ለማራመድ የሚያስችል እርምጃ መሆኑ ተገልጿል። በውይይቶቹም ከአቶ አለምአንተ አግደው በተጨማሪ በቤልጅየም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ፍርቱና ዲባኮ ፣ የኢትዮጵያ ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ማኔጅንግ ዳይሬክተር ኢንጂነር አንዋር ካሳሁን እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሙዎች ተሳትፈዋል።
በክልሉ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በጋራ መከላከል ይገባል
Mar 30, 2026 48
ጅግጅጋ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በጋራ መከላከል እንደሚገባ የክልሉ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ገለጸ። በሶማሌ ክልል በሴቶችና በህጻናት ላይ የሚደርሱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን የመከላከል ተግባርን ለማሳካት ያለመ ውይይት ተካሂዷል። የሶማሌ ክልል ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ሃላፊ ሀሊሞ ሀሰን በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ በሴቶችና በህጻናት ላይ የሚደርሱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የባለ ድርሻ አካላት ተሳትፎ መጠናከር አለበት። በክልሉ የሴቶች ፖለቲካዊና ማህበራዊ ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይሁንና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት አሁንም የዘርፉ ተግዳሮት መሆኑን ጠቁመዋል። ችግሩን በመፍታት ሁለንተናዊ ተሳትፏቸውን ለማጉላት ከምንግዜውም በላይ ለቅንጅታዊ አሰራር ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። የሶማሌ ክልል ሸሬአ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ አህመድ ሃዲ ሴቶች በጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ተጎጂ መሆናቸውን ተናግረዋል። ፍርድ ቤቱ ችግሩን ለመፍታት በሚደረጉ ጥረቶች የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን አመልክተዋል። የሶማሌ ክልል ፍትህ ቢሮ የቅሬታ የምርመራና ክስ ምስረታ የሥራ ሂደት ሃላፊ አቶ አብዲ አደን እንደገለጹት፣ በህገ-መንግስቱ የተደነገገውን የሴቶችና የህጻናት መብት መጠበቅ አስገዳጅ መሆኑን ገልጸዋል። በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚደርሱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችና ወንጀሎችን ለመከላከል የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሳደግ ሥራን ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሃዎ ሱሌማን በበኩላቸው በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችና ያለ እድሜ ጋብቻ በጤናቸው ላይ ጉዳት የሚያደርሱ በመሆናቸው በጋራ መከላከል ይገባል ብለዋል። በመድረኩ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የፍትህ አካላትና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ወጪን የቀነሰ እና እንግልትን ያስቀረ ዘመናዊ አገልግሎት ነው
Mar 30, 2026 65
ሐረር፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ወጪን የቀነሰ እና እንግልትን ያስቀረ ዘመናዊ አሰራር መሆኑን የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ። በሐረር ከተማ እየተሰጠ ያለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልገሎት በተመለከተ ኢዜአ ተገልጋዮችን፣ ሰራተኞችንና የሚመለከታቸውን የስራ ሃላፊዎች አነጋግሯል። አገለገሎት ሲጠቀሙ ካገኘናቸው ደንበኞች መካከል ወጣት ግርማ ተክሌ፤ በማዕከሉ በፍጥነትና በጥራት አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ወጪንና እንግልትን ያስቀረ፤ በዘመናዊ አሰራር የታገዘ መሆኑም እንዳስደሰታቸው ጠቅሰው፤ የተለያዩ ጉዳዮችን በአንድ ማዕከል በጥራትና ፍጥነት ማግኘት መቻል አዲስ የስራ ባህል ስለመሆኑም አንስቷል። ሌሎች ሲገለገሉ ያገኘናቸው አቶ ወንድዬ ዳሳለኝ እና አቶ ሙሉጌታ ታዬ፤ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጡ ዘመናዊ መሆኑን ገልጸዋል። የተለያዩ ጉዳዮችን አንድ ማዕከል ላይ በጥሩ መስተንግዶ አጠናቅቆ መመለስ መቻል የሚደነቅ አሰራር መሆኑን ጠቅሰው፤ ተገልጋዮቹ ይህንን አሰራር መንግስት ተግባራዊ በማድረጉ አመስግነዋል። በመሆኑም መሰል የአገልገሎት አሰጣጦች በሁሉም ከተሞች ቢተገበሩ የገንዘብ ወጪን የሚቀንስ፣ እንግልትንና ብልሹ አሰራርን የሚያስቀር ይሆናል ብለዋል። የሐረር ከተማ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሃላፊ አክረም መሀመድ፤ በማዕከሉ አሁን ላይ 35 የተለያዩ የአገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በርካታ ተገልጋዮች ያለውጣ ውረድ እየተስተናገዱ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በቀጣይም ተቋማትንና የአገልግሎት አይነቶችን ለመጨመር ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የሐረር ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልገሎት ክፍት የተደረገው ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም እንደነበር ይታወቃል።
ኢኮኖሚ
የአፋር ክልልን የቱሪስት መዳረሻዎች የበለጠ ለማልማት እና ለማስተዋወቅ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Mar 30, 2026 102
ሰመራ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ክልል የቱሪስት መዳረሻዎችን የበለጠ ለማልማት እና ለማስተዋወቅ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ። የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማስተዋወቅና በማልማት ረገድ ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል። የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ሁመድ እንደገለጹት የተደረገው ስምምነት ዘርፉን የበለጠ ለማስተዋወቅና ለማልማት ትልቅ እገዛ ያደርጋል። ስምምነቱ የአፋር ክልልን የቱሪዝም መዳረሻዎች ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችሉ በምርምር ላይ የተመሰረቱ ሥራዎችን ለማከናወንም ያግዛል ብለዋል። ቢሮው ዘርፉን የበለጠ ለማሳደግ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅት የሚያጠናክሩ እንቅስቃሴዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም በዘላቂነት ለማሳደግ የሚያስችል አሰራር ለማዘመን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መሐመድ ኡስማን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚቆየው ስምምነቱ የአፋርን ክልል ቱሪዝም ለማሳደግ ቁልፍ መሆኑን ጠቁመዋል። ዩኒቨርሲቲው ሁሉን አቀፍ የቱሪዝም ልማት ስትራቴጂ ማዘጋጀት፣ የቱሪስት መስህብ መረጃዎችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ ማድረግ እንዲሁም ዘመናዊ የቱሪስት መዳረሻ ካርታ እና የማስተዋወቂያ ሥራዎችን ያከናውናል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ ስምምነቱ የቱሪዝም ልማትን በምርምር ሥራዎች በመምራት ዓለም አቀፍ ደረጃውን እንዲጠብቁ ለማድረግም እንደሚያግዝ አመልክተዋል።
የቻይና የፋይናንስ ተቋማት ለኢትዮጵያ የልማትና ኢኮኖሚ ማሻሻያ ድጋፍ ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉ አረጋገጡ
Mar 30, 2026 56
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የቻይና የፋይናንስ ተቋማት ለኢትዮጵያ የልማትና የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስራዎች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታወቁ። በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የኢትዮጵያ ልዑክ በቻይና የስራ ጉብኝት እያደረገ ነው። ልዑኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ ነው። በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበውም የተገኙ ሲሆን፤ የልዑኩ ጉብኝት ሁለት አላማዎችን ያነገበ ነው። ይህም በሂደት ላይ ያለውን የዕዳ ሽግሽግ ድርድር ማጠናቀቅ እና ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ የሚውል የፋይናንስ ስምምነቶችን ማፋጠን ላይ ትኩረቱን አድርጓል። ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የቆየ የኢኮኖሚ አጋርነትም ይበልጥ እንደሚያጠናከር ተመላክቷል። ልዑካን ቡድኑ በቆይታው ከቻይና ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ፣ ከቻይና ኢንዱስትሪና ንግድ ባንክ እና ከቻይና ልማት ባንክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተከታታይ ውይይቶችን አድርጓል። ውይይቶቹ የዕዳ ሽግሽግ ሂደቱን በማጠናቀቅና ለኢትዮጵያ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንቶች አዲስ የፋይናንስ ምንጭ ለማግኘት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ናቸው። የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በዕዳ ሽግሽግ ድርድሩ ላይ ከፍተኛ መሻሻል መታየቱን ገልጸው፤ ሂደቱ አሁን ላይ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ መድረሱን አመልክተዋል። ይህ ሂደት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቅ ለመንግስት አስፈላጊውን የበጀት ነፃነት በመፍጠር፣ ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎችንና ዕድገት ተኮር የልማት ተግባራትን ለማፋጠን እንደሚያስችል ተናግረዋል። የቻይና የፋይናንስ ተቋማት በበኩላቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለውን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤቶች አድንቀዋል። መንግስት በዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ ላይ እያሳየ ያለውን ገንቢ ተሳትፎና የተመዘገበውን ስኬት በማድነቅ፣ ለኢትዮጵያ የልማትና የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረት የሚያደርጉትን ድጋፍ እንደሚቀጥሉ በድጋሚ አረጋግጠዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሩ የኢትዮጵያና የቻይናን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ጥንካሬ በማንሳት፣ የፋይናንስ ተቋማቱ ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚውለውን የፋይናንስ ማዕቀፍ የመገምገምና የማጽደቅ ሂደት እንዲያፋጥኑ ጥሪ አቅርበዋል። ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ፋይዳና አዋጭነት ያለው መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ ይህም ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የአቪዬሽን ማዕከልነት ለማጠናከርና ለረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ሽግግር ቁልፍ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። ሁለቱ ወገኖች በመሠረተ ልማት ፋይናንስና ኢኮኖሚ አጋርነት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከርም ተስማምተዋል። ይህም በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የቆየና የጋራ ተጠቃሚነትን መሠረት ያደረገ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው
Mar 30, 2026 99
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። በከተሞቹ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን አስተማማኝ ለማድረግ የዲስትሪቡሽን መስመር መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት በመከናወን ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ የኃይል ማከፋፈያ ኔትወርክ ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዙ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚወጡ መስመሮችን መልሶ መገንባትና ማሻሻል፤ እንዲሁም ከፈቃድ በላይ የሆነ የኃይል ፍጆታን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ 62 የሎድ ብሬክ ስዊቾችን መግጠምን ያካትታል። የሚገነቡት መስመሮች በኮንክሪት ምሰሶዎች እና በሽፍን ኬብል የሚከናወኑ በመሆናቸው ለአደጋ የማይጋለጡና ለረጅም ዓመታት አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ናቸው ተብሏል። የአዲስ አበባ ዲስትሪቢውሽን ሪሃቢሊቴሽን 4ኛ ምዕራፍ ፕሮጀክት ሃላፊ ቅድስት ላቀው ለኢዜአ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ በዋናነት የኃይል ኔትወርክ እድሳትን እና የመስመሮችን አስተማማኝነት ማረጋገጥን ዓላማ ያደረገ ነው። በዚህም 2 ሺህ አዲስ የተለያየ አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች ተከላና 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮች አቅም የማሳደግ ሥራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል፡፡ በፊዩዝ የነበረ ትራንስፎርመር ወጪ በዲስትሪቢዩሽን ቦክስ እንደሚሆን ተናግረው ይህም የሚቆራረጡ መስመሮች በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች 673 ኪሎሜትር የሚሆን መስመሮች እንደሚቀየሩ ገልጸው፤ ሽፋን የሌለው የኤሌክትሪክ መስመር ገመዶች እንደሚቀየሩና የኤሌክትሪክ መቆራረጥን እንደሚያስቀር ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ አስተማማኝ የሀይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል። የቻይና ኢነርጂ ግሩፕ ምክትል ማናጀር ሁ ዊሚንግ ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችን የማቆም ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ የማገናኘት እና የሙከራ ስራ መሆኑን ጠቁመዋል። በፕሮጀክቱ የሎት አንድ ሳይት መሀንዲስ አረአያ ጌታሁን በምስራቅ ሪጅን ካሉ ሳይቶች ውስጥ ሶስቱ መጠናቀቃቸውን ገልጸው፤ በተያዘለት ጊዜ ማጠናቀቅ የሚያስችል ስራም እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው
Mar 30, 2026 56
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ ማስፋፊያ ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ጀንበሬ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ በዞኑ ለሚገኙ 22 የሸማች ማህበራት የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርብ ተደርጓል። እስካሁን ባለው ሂደትም ከ580 ሺህ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት፣ ከ800 ኩንታል በላይ የዳቦ ዱቄት፣ ከ4 ሺህ 500 ኩንታል በላይ ስኳር ለተጠቃሚው እንዲደርስ መደረጉን ገልጸዋል። ጽሕፈት ቤቱ ለሚመጣው የትንሳኤ በዓል የዋጋ ንረትን ለመከላከል ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ጠቁመው በዚህም ከ20 ሺህ ኩንታል በላይ ጤፍ፣ የዳቦ ዱቄት፣ ስኳርና ሽንኩርት በህብረት ስራ አማካኝነት ለገበያ ለማቅረብ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ውጤቶችን ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ነው
Mar 30, 2026 100
ሮቤ፤ መጋቢት 21/2018(ኢዜአ)፦ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የሚከናወኑ የጥናትና ምርምር ውጤቶች ወደ ተጠቃሚው ማህበረሰብ እንዲደርሱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው ይህንን የገለጸው ''ምርምር ለማህበረሰብ ለውጥና ዘላቂ ልማት'' በሚል መሪ ሀሳብ ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ እያካሄደ ባለበት ወቅት ነው። በመርሐግብሩ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች፣ ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ከመማር ማስተማር ተግባር ጎን ለጎን የማህበረሰቡን ችግርና ፍላጎት መሰረት ላደረጉ ጥናትና ምርምሮች ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ዩኒቨርሲቲው በዋናነት በግብርና እና ምርታማነት፣ በቱሪዝም ልማት፣ በጤና ጥበቃ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ቀደም ሲል በተናጠል ይከናወኑ የነበሩ ጥናቶች አሁን ላይ ተቀናጅተው ጠንካራ ውጤት እንዲያመጡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በዚህ ዓመታዊ አውደ ጥናት ላይም በተለያዩ ዘርፎች የተጠኑ 42 የምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ጥናቶቹ በወረቀት ላይ ብቻ እንዳይቀሩ ከመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤቶችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅት መፈጠሩን ምክትል ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። ይህም የጥናትና ምርምር ውጤቶች ወደ ማህበረሰብ ፕሮጀክት ተቀይረው ህዝቡን በቀጥታ ተጠቃሚ እንዲያደርጉ ያስችላል ብለዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሀንድሶ(ዶ/ር) በበኩላቸው በበይነመረብ (ቨርቹዋል) ባስተላለፉት መልዕክት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን የምርምር ውጤቶች ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ የጀመሩትን ጥረት ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህም ተመራማሪዎች አቅማቸውን በማጎልበትና ምቹ መደላድሎችን በመጠቀም ውጤታማ ስራ ሊሰሩ እንደሚገባ አመልክተዋል። የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎችም እንዲህ ያሉ መድረኮች ተመራማሪዎችና ተጠቃሚ አካላት ተቀራርበው በችግሮች ላይ እንዲመካከሩ በማድረጋቸው፣ ለችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ጉልህ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።
የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀሎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመግታት ቅንጅታዊ አሰራሮች ይጠናከራሉ
Mar 28, 2026 155
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀሎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመግታት የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራሮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርአያስላሴ ገለጹ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው እና የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበርን መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው። "ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ስርዓት ለሀገር ዕድገት" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ባለው አውደ ጥናት ላይ የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበር በኢትዮጵያ ያለበትን ደረጃ የሚያሳይ የዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል። የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርአያስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ተግባራዊ በተደረገው የዲጂታል ፋይናንስ ስርዓት በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች ተገኝተዋል። ዲጂታል ስትራቴጂ 2025ን ጨምሮ በዲጂታል 2030 ለዲጂታል ፋይናንስ ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ገልጸው ይህም ለዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት በሚደረገው ሀገራዊ ጥረት ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም የዲጂታል ፋይናንስ ደህንነትን ለማስጠበቅና ከማጭበርበር ወንጀሎች ለመከላከል በትኩረት መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ይህንንም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመከላከል ቅንጅታዊ አሰራሮች እንደሚጠናከሩ አመልክተው፤ የፍትህ አካላት፣ የጸጥታና ደህንነት ተቋማትን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ ነው ብለዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው፤ አውደ ጥናቱ የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀለኞችን ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራትን ለማቀናጀት ያለመ መሆኑን አብራርተዋል። በአውደ ጥናቱ የጥናት ውጤቶችን መሰረት ያደረጉ የመፍትሔ ሃሳቦች ቀርበው በባለድርሻ አካላት ውይይት እንደሚደረግባቸውም ተናግረዋል። የህግ ክፍተቶችን መለየትና የቁጥጥር ስራዎችን ማጠናከር ሌላው የአውደ ጥናቱ ዓላማ መሆኑንም አስረድተዋል።
የኮደርስ ስልጠና ዲጂታል የፈጠራ ስራዎችን ለማሳደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Mar 28, 2026 117
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ዲጂታል የስራ ፈጠራ እድሎችን እና የፈጠራ ስራዎችን በማስፋት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን እያሳደገ መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአምስት ሚሊየን የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በተለይም ወጣቶች የእድሉ ተጠቃሚ ሆነው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ዜጎች ስልጠናውን እየወሰዱ ከራሳቸው አልፈው ለሀገራቸው የዲጂታል ልማት ስትራቴጂ ትግበራ አሻራቸውን እያኖሩ ይገኛሉ። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ስልጠናው የዜጎችን ዲጂታል ክህሎት በማሳደግ የአኗኗር ዘይቤን የሚያሳልጡ ክህሎቶችን ለማጎልበት ያስችላል። በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች ያላቸውን ክህሎት በማሳደግ ወደ ፈጠራ ስራዎች እንዲሸጋገሩ እገዛ አድርጓል ብለዋል። ይህም የሀገሪቱን ተወዳዳሪነት በማሳደግ ወደ እውቀት መር ኢኮኖሚ ለሚደረገው ሽግግር አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። በትምህርት፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝምና ሌሎች ዘርፎች በዲጂታል ስርዓት እንዲታገዙ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል። በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የአይ ሲቲ ዳይሬክተር ናኦል አንበሴ በበኩላቸው፤ በኢንስቲትዩቱ ተማሪዎችና ሰራተኞች ስልጠናውን እንዲወስዱ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ተጨማሪ ክህሎትን ለማጎልበት የሚረዳ በመሆኑ ዜጎች እድሉን በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል። የአይሲ ቲ ባለሙያዋ ጥሩ መልካም ስልጠናው በየትኛውም ሙያ የተሰማሩ ዜጎች ስራቸውን ለማሻሻል ያለውን ሚና ገልጻለች። ተማሪ ባዩሽ ተስፋዬ እና ከደቡብ ሱዳን የትምህርት ስኮላርሺፕ ተጠቃሚ የሆነው ላዱሊ ሞሪ ስልጠናው ከዲጂታል ዘመን ጋር አብሮ ለመራመድ ክህሎትን ለማሳደግ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኢኮኖሚው ምሶሶ እንዲሆን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር አለባቸው
Mar 27, 2026 441
ሮቤ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ ሳይንስና ቴክኖሎጂ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ መሪ ሚና እንዲጫወት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ ፈጠራና ኢንተርፕረነርሺፕ ላይ አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችና ግኝቶች ላሏቸው ወጣቶች ሲሰጥ የቆየውን ተግባር ተኮር ሥልጠና በማጠናቀቅ የእውቅና መርሐ ግብር አካሄዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ሳይንስና ቴክኖሎጂ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ መሪ ሚና እንዲጫወት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር ይገባቸዋል። ሚኒስቴሩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የኢኮኖሚው ምሶሶ እንዲሆን በሀገር ደረጃ የተቀረጸውን ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አክለዋል። በተለይ ክህሎትና አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብና ግኝት ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር ፕሮጀክቶቻቸው በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጣ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽንና የፈጠራ ምህዳርን በማስፋትና በዘርፉ የዳበረ ማህበረሰብ በመፍጠር ረገድ በተከናወኑ ሥራዎች አበረታች ለውጦች መታየታቸውን አመልክተዋል። በተለይ ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያበረታታ "ስታርት አፕ አክት" የተሰኘ የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖረውና የፋይናንስ ድጋፍ በማግኘት ወደ ኢኮኖሚ እንዲቀየር እየተደረገ መሆኑን በማሳያነት አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም በሀገር አቀፍ ደረጃ ባለፉት ዓመታት በዘርፉ የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ በማጠናከር ከወቅቱ ዓለም ዓቀፋዊ ሁኔታ ጋር የተናበበና በዘርፉ እመርታዊ ለውጥ ለማምጣት ያለመ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ ከመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችና ግኝቶች ላሏቸው ወጣቶች ያዘጋጀው የእውቅና መድረክ የዚሁ ጥረት አካልና ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ዩኒቨርሲቲው በባሌ፣ በምስራቅ ባሌና በምዕራብ አርሲ ዞኖች በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቴክኖሎጂ ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች በመመልመል የክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም በዩኒቨርሲቲው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል ሥልጠና ያገኙ ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በ2017 ዓ.ም በተካሄደው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውድድር አንደኛ ደረጃን በመያዝ ሽልማትና እውቅና ማግኘታቸው የዘርፉ ትኩረት ውጤት መሆኑን ለአብነት አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብና ግኝት ያላቸው ግለሰቦች በሥራቸው ስኬታማ እንዲሆኑና ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ተግዳሮቶችን እንዲረዱ የተሰጠው የአቅም ግንባታ ሥልጠና የጥረቱ አካል መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አክለዋል። እውቅና ያገኙ የፈጠራ ባለቤት የሆኑ ወጣቶች በበኩላቸው ያገኙት ተጨማሪ ዕውቀትና እውቅና የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሳቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ስፖርት
ካፍ የኢትዮጵያ እና የሳኦቶሜና ፕሪንሲፔ ጨዋታን 10 ሺህ ተመልካች ስታዲየም ተገኝቶ እንዲከታተለው ወሰነ
Mar 30, 2026 13
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሳኦቶሜና ፕሪንሲፔ አቻው ጋር የሚያደርገውን የ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ 10 ሺህ ተመልካች በድሬዳዋ ስታዲየም ተገኘቶ እንዲከታተለው መወሰኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። ካፍ የነገው የኢትዮጵያ እና ሳኦቶሜ ጨዋታ በዝግ እንዲካሄድ ውሳኔ አሳልፎ ነበር። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በስታዲየሙ ዙሪያ የተሰጡ የግምገማ አስተያየቶችን መሰረት በማድረግ በፍጥነት ለማስተካከል እርምጃ መውሰዱን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ከከተማ አስተዳደሩ እርምጃ ጎን ለጎን ጨዋታው ለተመልካች ክፍት እንዲሆን ባደረገው ከፍተኛ ጥረት እንዲሁም የካፍ ሴኪዩሪቲ ኦፊሰር በአካል ተገኝተው ከገመገሙ በኋላ በላኩት ሪፖርት መሰረት ካፍ 10 ሺህ ተመልካች በስታዲየም ተገኝቶ እንዲከታተል ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል። የሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታ ነገ ከቀኑ 10 ሰዓት በድሬዳዋ ስታዲየም ይካሄዳል።
ባስመዘገብነው የመጀመሪያ ድል ሳንዘናጋ የመልሱን ጨዋታ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንገባለን - አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ
Mar 30, 2026 60
ድሬዳዋ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ላይ ባገኘው ድል ሳይዘነጋ የመልሱን ጨዋታ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንደሚገባ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ተናገሩ። አሰልጣኝ ዮሐንስ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ የሚደረገውን የመልስ ጨዋታ አስመልክቶ ዛሬ በድሬዳዋ ስታዲየም ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። አሰልጣኙ በመግለጫቸው ዋልያዎቹ የቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታን ለማሸነፍ የሚያስችላቸውን ዝግጅት አድርገዋል ሲሉ ገልጸዋል። ዋልያዎቹ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ሞሮኮ ላይ ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ 3 ለ 0 ማሸነፋቸውን አስታውሰው፤ ይህ ውጤት በምንም መንገድ መዘናጋት ሳይፈጥር ነገ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንገባለን ብለዋል። የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች በጥሩ የማሸነፍ መንፈስ ታጅበው እንደሚጫወቱ ተናግረዋል። ተጫዋቾቹ በቂ ልምምድ ማካሄዳቸውንና በስነ-ልቦናም ጭምር ማሸነፍ የሚያስችላቸውን ዝግጅት ማድረጋቸውንም ነው የገለጹት። በአባቱ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት በመጀመሪያው ጨዋታ ያልነበረው የቡድኑ አምበል ጋቶች ፓኖም ለመልሱ ጨዋታ ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር በመቀላቀል ልምምድ ማድረጉን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ነገ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር የሚካሄደውን የ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ካሸነፈ ወደ ምድብ ድልድሉ ይቀላቀላል። 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምስራቅ አፍሪካ አገራት በሆኑት ኬንያ፣ ታንዛኒያ እና ዩጋንዳ ጣምራ አዘጋጅነት እ.አ.አ ጁን 2027 ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ
Mar 29, 2026 273
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ከመጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአደይ አበባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ሲካሄድ የቆየው 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ተጠናቋል። በሻምፒዮናው ላይ 36 ክለቦች፣ ተቋማት፣ 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተሳተፉ ሲሆን፤ 621 ወንድ፣ 436 ሴት በድምሩ 1057 ተወዳዳሪዎች ተሳትፈዋል። ሻምፒዮናው ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራት፣ ለአትሌቶች የውድድር እድል ለመፍጠር ፣ አትሌቶችን በሽልማት የማበረታታት ዓላማ ያለው ነው። በውድድሩ ማብቂያ ቀን 10 የፍጻሜ ውድድሮች ተካሄደዋል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሻምፒዮናው አጠቃላይ አሸናፊ በመሆን አጠናቋል። መቻል ሁለተኛ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው መጨረሳቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በሻምፒዮናው መዝጊያ ላይ የተገኙት የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን እና ሌሎች የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች ለክለቦች እና አትሌቶች የተዘጋጁ የገንዘብ፣ የዋንጫና ሜዳሊያ ሽልማቶችን አበርክተዋል። ፌዴሬሽኑ ለውድድሩ ለማካሄድ 10 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጉን አስታውቋል። ዘመናዊ የሰዓት መመዝገቢያ ማሽን (Time Tronics) በሻምፒዮናው ላይ ተግባራዊ ሆኗል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ፌዴሬሽኑ በየዓመቱ ከሚያካሂዳቸው ውድድሮች መካከል በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው።
ዋልያዎቹ ከሞሮኮ መልስ የመጀመሪያ ልምምዳቸውን አድርገዋል
Mar 29, 2026 188
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 20/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ለሚያደርገው የመልስ ጨዋታ የመጀመሪያ ልምምዱን ማምሻውን በድሬዳዋ ስታዲየም ሰርቷል። በአባቱ ድንገተኛ ህልፈተ ሕይወት ምክንያት በመጀመሪያው ጨዋታ ያልነበረው የብሔራዊ ቡድኑ አምበል ጋቶቾ ፓኖም ስብስቡን ተቀላቅሎ ልምምድ አድርጓል። የዋልያዎቹ ተጋጣሚ የሆኑት ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ዛሬ ከቀትር በኋላ ድሬዳዋ መግባታቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች የመልስ ጨዋታ ማክሰኞ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም ይካሄዳል። ኢትዮጵያ ከትናንት በስቲያ ሞሮኮ ላይ በተካሄደው የመጀመሪያ ጨዋታ 3 ለ 0 አሸንፋለች። በአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ የሚመራው ብሔራዊ ቡድን በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈ ወደ ምድብ ድልድል መግባቱን ያረጋግጣል። 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ በ2027 በታንዛንያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ ጣምራ አዘጋጅነት ይካሄዳል።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራ ለመስኖ ልማት መስፋፋት አመቺ ሁኔታን ፈጥሯል
Mar 30, 2026 75
ጎንደር መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ) :-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተካሄደው የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ስራ የከርሰ ምድር ውሃ አቅርቦትን በማሻሻል ለበጋ መስኖ ልማት መስፋፋት አመቺ ሁኔታ መፍጠሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ በአማራ ክልል የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራው ከ2003 ዓ/ም ጀምሮ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ይገልፃል። የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃውም የአፈር ክለትን በመቀነስ ውሃማ አካላትና የመስኖ መሰረተ ልማት በደለል እንዳይሞሉ በማድረግ የሰብል፣ የእንስሳትና ፍራፍሬ ምርታማነትን ለማሳደግ አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል። የመምሪያው ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ ለኢዜአ እንደገለጹት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተከናወነው የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት የለም አፈር መከላትን በማስቀረት ለሰብል ምርታማነት ማደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። ይህም የከርሰና ገጸ ምድር ውሃ አቅም እንዲጨምር በማድረግ አርሶ አደሩ በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ በመስኖ በማምረት የምግብ ሉዓላዊነቱን ለማረጋገጥ እየረዳው መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ ከአምስት ሄክታር በታች የነበረውን ዓመታዊ የመስኖ ልማት ስራ አሁን ላይ ወደ 40 ሺህ ሄክታር መሬት በመስኖ እንዲለማ የሚያስችል ውጤት ማስገኘቱን አስረድተዋል፡፡ በዞኑ ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ተጠብቀው እየለሙ የሚገኙ ተፋሰሶች ቁጥር 955 መድረሱን ጠቁመው ይህም የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ እንዲሳካ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል። አሁን ላይ በንብ ማነብ፣ በእንስሳት ማድለብና በወተት ላሞች እርባታ ለተሰማሩ 1 ሺህ 350 ወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ በዘንድሮ በጋም በድግግሞሽ ከ11 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ባካሄዱት የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ 57 ሺህ 370 ሄክታር የተራቆተ መሬት ላይ የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ማከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ የጎንደር ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ሰጠኝ አለነ እንደገለጹት በበጋው የምናከናውነው የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ስራ በመስኖ፣ በእንስሳትና በሰብል ልማት ምርታማነታቸው እንዲያድግ አስችሏል። በበጋ መስኖ በመታገዝ በአንድ ሄክታር መሬታቸው ላይ ቲማቲም፣ ሽንኩርትና ጥቅል ጎመን አምርተው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስቻላቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የጭልጋ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር እሱባለው መሳፍንት በበኩላቸው በለሙ ተፋሰሶች ላይ በ15 ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች ታግዘው ማር አምርተው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራ የህልውናችን መሰረት መሆኑን በመገንዘባችን በልማት ቡድኖች ተደራጅተን በየዓመቱ በግልና በወል መሬቶች ላይ የእርከንና ክትር ስራዎችን እያከናወንን እንገኛለን ብለዋል፡፡
የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ የብዝኃ ሕይወት ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል ያስችላል
Mar 29, 2026 208
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 20/2018 (ኢዜአ)፡- የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ የብዝኃ ሕይወት ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል ገንቢ ሚና እንዳለው የዘርፉ ምሁራን ገለጹ፡፡ በአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የአካባቢ ሕጎችና ደረጃዎች ዴስክ ኃላፊ ወንደሰን ታደሰ፤ ኢትዮጵያ የውኃ፣ የደን፣ የዓየር ንብረት አገልግሎት፣ የቁጥጥርና ቱሪዝም ሥርዓተ-ምኅዳር ብትታደልም በሚገባት ልክ አልተጠቀመችም ብለዋል። የሥርዓተ-ምኅዳር ጉዳዮች በሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ጉዳዮች በከፍተኛ ጫና ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ በአገልግሎቱ አቅራቢዎችና ተጠቃሚዎች መካከል የጋራ መግባባትን በመፍጠር ዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሥርዓትን ማጠናከር እንደሚያስችልም አስረድተዋል። የፋርም አፍሪካ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሸዊት አማኑኤል በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያን የብዝኃ ሕይወት ሃብቶች ለሕብረተሰቡ ይበልጥ ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚያስችል ሥራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የባሌ አካባቢ ማኅበረሰብ ተፈጥሮን በመንከባከብ የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ተጠቃሚ መሆን መጀመሩን ገልጸው፤ ይህ በሁሉም አካባቢዎች መስፋት እንዳለበት አመላክተዋል። መንግሥት በአረንጓዴ ዐሻራና በአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገቡን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ያላትን የብዝኃ ሕይወት ሀብት ይበልጥ መለየትና ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የውኃ ሀብትና ሀይድሮሎጂ መምህር ዓለምአየሁ አባተ (ዶ/ር)፤ የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ አዋጅ ማኅበረሰቡ የሠራበትን እንዲያገኝ በማድረግ የተጠናከረ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ማከናወን ያስችላል ብለዋል፡፡ በባሌ ኢኮሎጂ በ20 ወረዳዎች በመሰማራት እየሠሩ መሆኑን የገለጹት የፋርም አፍሪካ ፕሮግራም ሥራ አስኪያጅ ፈይሳ አሰፋ፤ በኢትዮጵያ የካርበን ክፍያ መጀመሩ የሕብረተሰቡን የአካባቢ ጥበቃ ተነሳሽነት ያሳድጋል ብለዋል፡፡ የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ አዋጁ ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የብዝኃ ሕይወት ሀብት ጠብቃ እንድትቆይና ማኅበረሰቡ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኝ ያስችላል ሲሉም አስገንዝበዋል።
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ችግኞች ዝግጅት በስፋት እየተከናወነ ነው
Mar 28, 2026 111
አምቦ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ችግኞች ዝግጅት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። በጽህፈት ቤት የደን ልማት ባለሙያ ጉደታ ጡሪ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ እየተዘጋጁ ከሚገኙ ችግኞች መካከል ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ዝርያዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል። በክረምቱ ወራት አጠቃላይ ከ94 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የችግኝ ተከላ እንደሚከናወን ገልጸው፤ የችግኝ ማፍላት ስራው በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ዝግጅቱ የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንዲቻል ምርታማነታቸው ከፍተኛ በሆኑና በተሻሻሉ የችግኝ ዝርያዎች ላይ ትኩረት ማድረጉንም ጠቅሰዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሮች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተው፤ ችግኞችን የመንከባከብና የመጠበቅ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑንም አክለዋል። የተተከሉ ችግኞች የአካባቢ ስነ-ምህዳርን ከመቀየር አንጻር ከፍተኛ ሚና ከመጫወታቸው ባለፈ፣ ደርቀው የነበሩ ኩሬዎች ዳግም ውሃ እንዲይዙ በማድረግ ለአርሶ አደሩ ምቹ ሁኔታ ፈጥረዋል ነው ያሉት። ባለፉት ሰባት ዓመታት በድምሩ 616 ሺህ 613 ሄክታር መሬት ላይ ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰው፤ የአካባቢው ማህበረሰብ ያለውን ደን የመጠበቅ ባህላዊ እሴት ለአረንጓዴ ልማት ስራው ስኬታማነት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ገልጸዋል።
ለቀጣዩ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የችግኝ ዝግጅት እየተከናወነ ነው
Mar 27, 2026 105
ሆሳዕና፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ ሻራ መርሐ-ግብር የችግኝ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ አስታውቋል። የቢሮው ኃላፊ አብርሃም መጫ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ባለፉት 7 ዓመታት በክልሉ 450 ሺህ ሔክታር በአካባቢ ጥበቃና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ማልማት ተችሏል። በዚህም የአፈር ለምነትን በማስጠበቅ፣ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥን ጨምሮ በበርካታ ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አብራርተዋል። በዚህ ዓመትም 270 ሚሊየን የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል 80 ሺህ ሔክታር መሬትን ለማልማት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራን ነው ብለዋል። ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ ለምግብነትና ለሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የሚውሉ ችግኞችን የማፍላትና የማዘጋጀቱ ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝም ነው ያረጋገጡት።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 472
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው
Mar 22, 2026 166
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
የኢጋድ እና ጃፓን ትብብር መጠናከር ለቀጣናዊ ሰላም የጎላ ሚና አለው
Mar 9, 2026 274
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ጃፓን በቀጣናው ሰላም ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሠሩ ገለጹ። የኢጋድ ምክትል ዋና ፀሐፊ መሐመድ አብዲ ዋሬ ከጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ዳይሬክተር ሂሮኒሪ ሱዙኪ ጋር በጅቡቲ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በኢጋድ ቀጣና ስላለው የሰላም እና ደኅንነት ሁኔታ ሐሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቀጣይም ትብብራቸውን በይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሠሩ ማረጋገጣቸውን ኢጋድ ሴክሬተሪያት መረጃ ጠቁሟል። ጃፓን ለኢጋድ እና አባል ሀገራት፤ በቀጣናው ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት መረጋገጥ ሥራ ዋና አጋር ሆና መቀጠሏም ተመላክቷል።
ሀገራት የሴቶች መብቶችን የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባቸዋል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Mar 9, 2026 286
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የሴቶች መብቶች እና የሥርዓተ ጾታ እኩልነነት የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን እንዲወስዱ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጥሪ አቀረቡ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። "መብቶች፣ ፍትሕ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሐሳብ ነው። የአፍሪካ ኀብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም፤ ቀኑ የአፍሪካ ሴቶች እና ልጃገረድ ስኬቶችን የምናከብርበት፣ ሴቶችን ማብቃት እና ጥበቃ ላይ የገባናቸውን ቃል ኪዳኖች ዳግም የምናድስበት ነው ብለዋል። ሴቶች በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ከአመራር ሰጪነት እስከ ቴክኒካዊ ቦታዎች ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም አመልክተዋል። የሥርዓተ ጾታ እኩልነት የተቋሙ ሥራ ማዕከል መሆኑንም አስረድተዋል። የአፍሪካ ኅብረትም ቀኑን እያከበረ ሲሆን፤ የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር በአፍሪካ የሴቶችን መብቶች የሚደግፉ ቁልፍ ማዕቀፎችን በዚሁ ወቅት አንስተዋል። ለአብነትም የአፍሪካ ኅብረት የሰው እና ዜጎች መብቶች ቻርተር የሴቶች መብቶች የሕግ ማዕቀፍ፣ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) እና የሴቶችና ልጃገረዶች ጥቃትን ማስቆም ያለመውን የኅብረቱ ን ኮንቬንሽን በማሳያነት ጠቅሰዋል። የኮንቬንሽኑ ወደ ትግበራ መግባት ትልቅ ስኬት እንደሆነ ገልጸው፤ ሀገራት በሕግ አውጪ ምክር ቤት ማዕቀፉን በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲያስገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ሊቀ መንበሩ የሥርዓተ ጾታ እኩልነት እና የልማት የትኩረት መስኮች ቁርኝት እንዳለውም አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የ2026 ትኩረት በሆነው ውኃ እና ንጽህና ጋር በተያያዘ፤ ሀገራት የሴቶችን ጫና የሚያቃልሉ እና ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን እንዲያከናውኑም ጥሪ አቅርበዋል።
ሐተታዎች
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3362
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … በኢዜአ ዐይን …! የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 374
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 434
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 403
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት
Mar 28, 2026 261
ከመጋቢት 13 እስከ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • የ ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን እና የሰው ልጅ ታሪክ በጀመረበት ምድር የተገነባውን ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅት ሎጁ የዛሬ 50 እና 60 ዓመት መሠራት የነበረበት ቢሆንም፤ አሁን ስለዘገየን አንቆጭም ማለታቸው ይታወሳል። ይህን ስለሠራንም አንረካም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሩጫችን ገና ብዙ እንደሆነ፣ አፋር ገና እንዳልተነካ አስበን ይህን ጅማሮ ይበልጥ በማላቅ ለማስቀጠል እንተጋለን ሲሉም ተናግረዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከቃና ቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነም ገለጻ አድርገዋል። እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸውን ፋይዳም አንስተዋል። • ኢትዮጵያ በማላቦው ጉባዔ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ ወደ ማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ማላቦ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑዌል ኡሳ ኡዙዌን ጨምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጉባዔው ከመጋቢት 18 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ ሲሆን እስከ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቀጥላል። • የልማት ሥራዎች ጉብኝት በባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የባሕር ዳር ከተማን የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያጎሉና ግንባታቸው እየተፋጠኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ መሠረተ-ልማት እና የአየር መንገድ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገታችን የጎላ ፋይዳ ይኖራቸዋል ሲሉም በወቅቱ ገልጸዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጎንደርን የውኃ ጥም ይቆርጣል፤ የገበሬውን መሬት ያጠጣል፤ የአካባቢውን ምኅዳር ይለውጣል የተባለው የመገጭ የመጠጥ ውኃ ግድብ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተዋል። በዚሁ ወቅት የሀገር ሀብት ፈስሶባቸው መክነው እና ባክነው የቀሩ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ከሞት እያስነሡ ማፋጠን የዚህ መንግሥት ልዩ መለያው ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም የመገጭ ግድብ ምስክር መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ሳይና ሳቢያ የገጠር ቀበሌ የተገነቡ የገጠር ኮሪደር ሞዴል ቤቶችን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም በአንድ ወር የግንባታ ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀው ይህ ሞዴል መንደር በአካባቢው ለረጅም ዓመታት የቆየውን የጤና ጣቢያ፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎት ጥያቄ በተግባር መልሷል ብለዋል። በሀገራችን ከተማው ብቻ ሳይሆን ገጠሩም እኩል እየተዋበ፣ በልማት እየተገነባና በዕድገት ፍኖት ላይ በጽኑ መሠረት እየተራመደ ይገኛልም ነው ያሉት። ይህ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የማሸጋገር ትልቁ ማሳያችን ነው ሲሉም ገልጸዋል። • "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ በአዲስ አበባ 4ኛው "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም፤ የምንፈልገው ድጋፍን ሳይሆን አጋርነትን ነው፤ እርዳታን ሳይሆን ኢንቨስትመንትን ነው! ለባለ ሀብቶች ምቹ፣ ግልጽና ተራማጅ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ አዘጋጅተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ካፒታል፣ ለችሎታ እና ለዕድል በሯን ወለል አድርጋ መክፈቷንም አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ አሁን በፍጥነት ወደ ከፍታ እየገሠገሠች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ የዕድገት ጉዞ፤ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ባለ ሀብቶች ኢትዮጵያ ለእናንተ ዝግጁ የሆነ፣ በዕድሎችና በስኬቶች የተሞላ ታላቅ የኢንቨስትመንት መሶብ አላት፤ ኑ አብረን እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል! • የትግራይ ክልል አጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በሰጡት መግለጫም፤ ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ለመጀመርና ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል። በዚህም ከክልሉ ጊዜያዊ አሥተዳደር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀሌ እና በአዲስ አበባ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ጥረቶች ውስጥ ሂደቱን በክልሉ ለማካሄድ የሚያስችሉ አስቻይ ሁኔታዎች ባለመፈጠራቸው፤ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች ምርጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ እንዲከናወን መወሰኑንም አስረድተዋል።
ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት
Mar 26, 2026 141
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በኋላ የታዛቢነት (Observer) ደረጃን አገኝታለች። እ.ኤ.አ በ2006 የውጭ ንግድ ፖሊሲዋን የሚገልጽ ሰነድ ለድርጅቱ አቅርባለች። ሰነዱ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች፣ የወጪና ገቢ ንግድ ሕጎች፣ የቀረጥ፣ ከቀረጥ ውጭ ያሉ የንግድ ገደቦች፣ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ እና የኢንቨስትመንት ሕጎችን ያካተተ ነበር። በኢትዮጵያ እና በዓለም ንግድ ድርጅት መካከል የመጀመሪያው የድርድር ምዕራፍ የተጀመረው እ.አ.አ በ2008 ነው። ከእ.አ.አ 2008 እስከ 2012 በቆየው የቴክኒክ ድርድር ሶስት የስራ ቡድን ስብስባዎች ተካሂደዋል። በዚህ ወቅት የነበረው ድርድር በዋናነት ኢትዮጵያ ስለ ንግድ ሥርዓቷ ማብራሪያ የምትሰጥባቸው እንጂ፣ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘት አልቻሉም። ከእ.አ.አ 2012 እስከ 2019 የሁለቱ ወገኖች ድርድር ተቋርጦ ነበር፤ ለሰባት ዓመታት እንዲቋረጥ ያደረጉ የተለያዩ ምክንያቶች ይነሳሉ። በወቅቱ ስልጣን የነበረው የኢህአዴግ መንግስት "የገበያ ውድቀት" አለ ብሎ ያምን ነበር። ስለዚህም እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም እና ኢነርጂ ያሉ ስትራቴጂካዊ ዘርፎች በመንግስት እጅ መቆየት አለባቸው የሚል አቋም ነበረው። ይህ የመንግስት ጽንሰ ሀሳብ ድርጅቱ የተለያዩ ዘርፎች ለውጭ ክፍት መደረግ አለባቸው ከሚለው አቋም ጋር የሚጣጣም አልነበረም። በዓለም ንግድ ድርጅት የተጠየቁ የንግድ ስርዓትን የማዘመን ስራዎች በሚፈለገው መልኩ አለመሄዳቸውም ለድርድሩ መቆም እንደ ምክንያትነት ይነሳል። የለውጡ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ የአባልነት ድርድር በድጋሚ ነፍስ ዘርቷል። መንግስት በተለያዩ ዘርፎች የወሰዳቸው ጠንካራ የንግድ እና ኢኮኖሚ እርምጃዎች ድርድሩ በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀጥል አድርጓታል። መንግስት እንደ ቴሌኮም፣ ባንክ እና ሎጅቲክስ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉ በድርጅቱ እንደ ትልቅ ለውጥ የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያን ሕጎች ከድርጅቱ ህጎች ጋር የማጣጣም ስራም ተከናውኗል። ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለው የንግድ ሕግ ማሻሻያ ተደርጎበት ዘመናዊ የንግድ አይነቶች የተካተቱ ሲሆኑ፤ የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መቋቋም የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ላይ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል። ኢትዮጵያ የሸቀጦች ታሪፍ ቅናሽ ሰነዷን አሻሽላ አቅርባለች። ይህም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች የምትጥለው ቀረጥ በምን ያህል መጠንና በስንት ዓመት ውስጥ እንደሚቀንስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የገባችውን ቃል በተግባር ያሳየችበት ነው። በአሁኑ ሰዓት በዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ኢትዮጵያ በተናጠል እንደ ቻይና፣ ሩሲያ፣ አሜሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችና ካናዳ ካሉ ሀገራት እና ከአውሮፓ ህብረት ጋር የገበያ ተደራሽነት ድርድር እያደረገች ነው። በተደረጉት የተናጥል ድርድሮች ላይም ለኢትዮጵያ አባልነት ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። ከአዕምሯዊ ንብረት ጋር በተያያዘ የፈጠራ ውጤቶችን፣ የንግድ ምልክቶችን እና የባህል እሴቶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ ሕግና ተቋም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጓል። የጉምሩክ አሰራር የሸቀጦችን ፍሰት ለማሳለጥ የዲጂታል ጉምሩክ አሰራርን የማስፋፋት ስራ በመንግስት በኩል ተከናውኗል። 14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ስብስባ ከመጋቢት 17 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በካሜሮን ያውንዴ መካሄድ ጀምሯል። በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክም በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ያውንዴ ገብቷል። ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከስብስባው ጎን ለጎን የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን ሚኒስትሩ ከዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ (ዶ/ር) ጋር ያደረጉት ውይይትም በዋናነት የሚጠቀስ ነው። በውይይቱ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለድርጅቱ አባል አገራት ከ1200 በላይ ለሚሆኑ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠቷንና ከ419 በላይ የሕግና የፖሊሲ ይዘቶችን ማሳወቋን ጠቁመዋል። የያውንዴው ስብስባ ለኢትዮጵያ የአባልነት ጉዞ የፖለቲካ ድጋፍን ለማሰባሰብ ያስችላታል። በቅርቡ የድርጅቱ አባል ከሆኑ የአፍሪካ እና ሌሎች ሀገራት ጋር የቴክኒክ እና የተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግም ምቹ አጋጣሚ ይፈጥርላታል። የያውንዴው ውይይት ኢትዮጵያ በቴክኒክ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ ደረጃም ለድርድር ዝግጁ መሆኗን የምታሳይበት ነው። የዓለም የንግድ ድርጅት እ.አ.አ በ1995 የተቋቋመ ሲሆን ዋና መቀመጫው ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ነው።ድርጅቱ 166 አባል ሀገራት አሉት። አባል ሀገራቱ የዓለምን 98 በመቶ የንግድ ልውውጥን እንደሚሸፍኑ መረጃዎች ያመለክታሉ። የዓለም ንግድ ድርጅት በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው አቅምና ተጽዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው። ድርጅቱ ራሱ ገንዘብ የሚያበድር ባንክ ባይሆንም፣ የዓለምን የንግድ “የጨዋታ ሕግ" በመቅረጽ ረገድ ያለው ሚና ትልቅ መሆኑን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል መሆኗ የገበያ እድሏ እንዲሰፋ ያደርጋል። የኢትዮጵያ ምርቶች በ160+ አባል አገራት ገበያ ውስጥ ያለ አድሎና በዝቅተኛ ታሪፍ እንዲገቡ ዕድል ይሰጣል። ይህ በተለይም ለግብርና ውጤቶችና ለጨርቃጨርቅ ምርቶች ትልቅ በር ይከፍታል። የኢትዮጵያ አባል መሆን ሀገሪቷ ዓለም አቀፍ የንግድ ሕጎችን እንደምታከብር ማረጋገጫ ስለሚሆን፤ ትልልቅ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸው እምነት እንዲጨምር ያደርጋል። ኢትዮጵያ አባል መሆኗ ከሌሎች አገራት ጋር የንግድ አለመግባባቶች ቢገጥሟት፣ በድርጅቱ የክርክር መፍቻ መድረክ አማካኝነት መብቷን ማስከበር ትችላለች። ኢትዮጵያ የንግድ አቅሟን ለመገንባት የሚያግዙ ልዩ ልዩ ሥልጠናዎችንና የቴክኒክ ድጋፎችን ከድርጅቱ ማግኘት ትችላለች። ኢትዮጵያ በያዘችው ፍጥነት እና ቁርጠኝነት ከቀጠለች እ.አ.አ 2026 የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድሯን የማጠናቀቅ እድሏ ሰፊ ነው። የድርድሩ መጠናቀቅ ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማጽደቅ እና የአገር ውስጥ ህጎችን ከድርጅቱ ሕግ ጋር የማጣጣም ስራዎችን ጨምሮ በቀጣይ ምዕራፍ ለሚከናወኑ ስራዎች በር ይከፍታል። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን ውጥኗ ከ23 ዓመታት በኋላ እውን ሊሆን የተቃረበ ሲሆን ድርድሩም ወደ መደምደሚያው ምዕራፍ ደርሷል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 761
ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል የነዳጅ ብክነትን ለመቀነስ ምን ዓይነት ብልኀት መጠቀም ይመከራል? ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 21, 2026 238
በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ (በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት ስትወጥን የቀደመ ወረቷን፤ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶቿን ይዛ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን ቀረጸች። ይህን ዕውን ለማድረግ ስትዘይድም የሕዝቧን የፋይናንስ፣ የዕውቀት እና የጉልበት ዐቅም በመደመር መጠቀምን ሻተች። በዚህም መሠረት በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶችን አስመዘገበች። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። በኢዜአ ዐይን …! ✍️ ገበታ ለሸገር በአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻዎችና መናፈሻዎችን ለማልማት በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገው ገበታ ለሸገር ኢኒሼቲቭ፤ ከእንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ወንዝ ያለውን የሚሸፍን ነው። የሚሠራበትን ገንዘብ ለማሰባሰብም የገበታ ለሸገር የእራት ምሽት በዳግማዊ አጼ ምኒልክ የግብር አዳራሽ ተዘጋጀ፤ ባለሀብቶች፣ የንግድ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ጨምሮ ዓለም አቀፍና አኅጉራዊ ድርጅቶችም ተሳትፈዋል። ኢኒሼቲቩ አንድነት ፓርክን ጨምሮ የእንጦጦ መናፈሻንና ሌሎች የተለያዩ መዲናዋን ያስዋቡ በረከቶችን ችሯል። ይህም የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት በርካታ ቱሪስቶችን ከመሳብ ባለፈ፤ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለምጣኔ ሃብት ዕድገት ጉልኅ አስተዋጽዖ አበርክቷል። ለዚህ ሁሉ ስኬት መነሻ የሆኑትን ጉዳዮች ያስጀመሩትም ያስፈጸሙትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በገበታ ለሸገር የተገኙ ውጤቶችን መነሻ በማድረግ ገበታ ለሀገር የተሰኘውን ኢኒሼቲቭ አበሠሩ። ✍️ ገበታ ለሀገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነሐሴ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻን ለማልማት ያለመ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጅተዋል። ይህም በአዲስ አበባ ከተሠራው ገበታ ለሸገር ቀጥሎ የተከናወነ ነው። በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የገበታ ለሀገር ዓላማ የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ የቱሪስት መስኅብ የሚሆኑና የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ አካባቢዎችን ማዘጋጀት መሆኑን አስገንዝበዋል። በገበታ ለሀገር መርሐ-ግብር ባለሀብቶችን ጨምሮ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ 3 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህን ለማሳካት የሀገሪቱን ባለሃብቶች፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በተለያዩ መርሐ-ግብሮች የተሳተፉበት የገቢ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ውጤታማ ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገበታ ለሀገር ውጥን፤ እንደ ሀላላ ኬላ፣ ጨበራ ጩርጩራ፣ ወንጪ እና ጎርጎራ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና የተፈጥሮ ሀብቶችን አጉልተው በማሳየት ይበል ያሰኘ ውጤት አስመዝግቧል። ✍️ ገበታ ለትውልድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2015 ዓ.ም ገበታ ለትውልድ የተሰኘ ኢኒሼቲቭ ይፋ ያደረጉ ሲሆን፤ ይህም ተጨማሪ መዳረሻዎች እንዲለሙ አስችሏል። በዚህ ኢኒሼቲቭ ሥር በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች የመዳረሻ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል፤ እየተከናወኑም ነው። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዳሴ ግድብ አካባቢና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የፕሮጀክቱ አካል የሆኑ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራዎች እየለሙ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውን የሸበሌ ሪዞርት በይፋ መርቀዋል። እያንዳንዱ የሪዞርቱ ገጽታ የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ባህላዊ ሐብት የሚያንፀባርቅ ነው። ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በሚደረገው ጉዞ ትልቅ ታሪካዊ እጥፋት እንደሆነም ተገልጿል። ሎጎ ሐይቅ ሪዞርትም ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመረቀ ሲሆን፤ ለጎብኚዎች የማይረሳ ትውስታን የሚሰጥ እጅግ ማራኪ ቦታ ሆኖ ቀርቧል። ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለመሆን ያላትን ቁርጠኝነትና ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ቋሚ ምስክርም ነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት። የቱሪዝም ልማቱን ከተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ፣ ከዘላቂነትና ከአካታችነት ጋር በማቀናጀት፤ ሪዞርቱ የወሎ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ዕሴት ለዓለም ማኅበረሰብ የሚያስተዋውቅበት ሰፊ ገበታ ሆኖ ያገለግላል። ታሪካዊ ቦታዎችና የሀገር መገለጫ መሠረተ-ልማቶች ብሔራዊ ትርክቶችንም የሚገነቡ ናቸው። በአጠቃላይ እነዚህ ሁሉ ጥረቶች ለአካባቢ ጥበቃ ቅድሚያ በመስጠት ብሎም በየአካባቢው የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል። የቱሪዝም ዘርፉን ለማጎልበት፣ ብዙ ጎብኚዎችን ለመሳብ፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማጠናከር፣ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው። እንዲሁም ነባር ቅርሶችን በማደስና በመጠገን ለትውልድ ለማሻገር ደማቅ ዐሻራ አሳርፈዋል። በሌላ በኩል የቱሪዝም መዳረሻዎችን ማልማት የመንግሥት ብቻ እንዳልሆነ ዐሳይተዋል። ባለሀብቶችና ሌሎች የማኅበረሰብ ክፍሎችም ሀገራቸውን የመሥራት ሚና እንደሚጠበቅባቸው አሥተምረዋል። ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት ብሎም በርካታ የሥራ ዕድሎች በመፍጠር በኢኮኖሚው ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በኢትዮጵያም ቱሪዝም መንግሥት ላስጀመረው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የማዕዘን ድንጋይ ነው። ከአምስቱ ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎችም አንዱ የሆነው ለዚህ ነው። መሠረተ-ልማቶች ከሚገነቡባቸው ጡቦች ባለፈ የነገን ሀገራዊ ማንነት፣ ራዕይ እና መዳረሻን ይበይናሉ። ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ እንኳንም ታሰቡ፤ እንኳንም ተሳኩ። ይህ ባይሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ተጨማሪ መዳረሻ ባላገኘች ነበር።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3765
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2536
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8328
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6816
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 29, 2026 2824
በዮሐንስ ደርበው ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ በያዝነው ዓመት ወርኃ ግንቦት በባተ 24ኛው ቀን ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ቀን ቆርጣለች። ለዚህም ቅድመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅና የጊዜ ሰሌዳ በማውጣት ወደ ትግበራ ምዕራፍ ገብታለች። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን ተዓማኒ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን፤ ቀሪ ሥራዎችም እየተከናወኑ መሆኑን ገልጿል። ለዚህም የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ መግባታቸው በአሥረጂነት ይጠቀሳሉ። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ መሰጠቱ፤የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ የሀገር ውስጥ ድርጅቶች በኦንላይን ሥርዓት በታዛቢነት መመዝገባቸውን አስረድቷል። በኢዜአ ዐይን …! በገበታ ለሀገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የጤና ነገር … እንዲሁም ዐለም ዐቀፍ ታዛቢዎች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካኝነት መጥተው ፈቃድ የሚወስዱበት ዝግጅት እየተደረገ ነው። ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ምዝገባ አወዳድሮና ገለልተኝነታቸውን በፖለቲካ ፓርቲዎች አስተችቶ ያሠለጠናቸውን 187 ሺህ 28 የምርጫ አስፈጻሚዎች አሠማርቷል። ለመራጮች ምዝገባ የተዘጋጁ 46 ሺህ 757 ጣቢያዎች እና ተጨማሪ በርካታ ንዑስ ጣቢያዎችም ተሠናድተዋል። እንደ ምርጫ ቦርድ መረጃ፤ 46 የፖለቲካ ፓርቲዎች በዘንድሮው ምርጫ ለውድድር ተመዝግበዋል። በሌላ በኩል ደግሞ 73 ዕጩዎች በግል ለውድድር መቅረባቸው ተገልጿል። ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊና ፍትሐዊ ሆኖ የሚከናወነው ሁሉም ፓርቲ ሕግን አክብሮ ኃላፊነቱን ሲወጣ እንደሆነ ያስማማል። የምርጫው ስኬት የሚረጋገጠውም ቦርዱ ለብቻው በሚያደርገው ጥረት ሳይሆን፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ዕኩል ኃላፊነቱን መወጣት ሲችል መሆኑ ይታመናል። በመሆኑም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰባት ምዕራፎችና በ30 አንቀጾች የቀረበውን የምርጫ ሥነ-ምግባር ደንብ ፈርመዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ሂደት የዜጎችን ተሳትፎ ለማበረታታት “ምርጫችን ነው-ሀገር ያለኛ” የተሰኘ የምርጫ ኅብረ-ዝማሬ ማስመረቁ ይታወቃል። በዚሁ ወቅት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ ኅብረ-ዝማሬው አካታች ተሣትፎን ለማበረታታት መሠናዳቱን አስገንዝበዋል። የልዩ ልዩ ድምጾች ኅብራዊነት ያለውን የጋራ ጥንካሬ በማሳየት በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የዜጎችን ተሳትፎ ማጎልበት የኅብረ-ዝማሬው ዓላማ መሆኑም ተገልጿል። በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫም “የሀገር ካስማ” የተሰኘ ኅብረ-ዝማሬ ይፋ መደረጉ ይታወሳል። ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ነው። እስካሁን ባለው መረጃ ምዝገባው እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ይቀጥላል። የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ የሚገኘውም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ ነው። ከአጠቃላይ የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17 ሺህ ያህሉ የዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ ለማድረግ ሲሠራ መቆየቱን ቦርዱ ማሳወቁ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በማንዋልና በዲጂታል አማራጭ በተከናወነ የመራጮች ምዝገባ ከ28 ሚሊየን 365 ሺህ 310 በላይ መራጮች ተመዝግበዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 37(7) ላይ ቦርዱ በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የዕጩዎች ምሥልና የመለያ ምልክቶችን አቀማመጥ፣ ቅደም ተከተልና እንዲሁም ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች እና የግል ዕጩዎች ግልጽ በሆነ መንገድ በመመሪያ እንደሚወስን ይደነግጋል። በዚህም መሠረት ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚኖራቸውን ቅደም ተከተል ለመወሠን የሚያስችለውን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ባሳለፍነው መጋቢት 14 ቀን በይፋ አስጀምሯል። የድምፅ መስጫ ወረቀት ኅትመት የሚከናወነው በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የዕጩዎች ምሥልና የመለያ ምልክት አቀማመጥን የሚወሥነው የዕጣ ማውጣት ሂደት መጠናቀቅን ተከትሎ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሠዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሂዷል። በዚህም መሠረት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የዓየር ሠዓት ተድልድሎላቸዋል። የሠዓት ድልድሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውንና ፖሊሲዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የግል ዕጩዎችም አማራጭ ሐሳባቻቸውን እንዲያጋሩና የምርጫ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ ብሎም ከመራጩ ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል የሚሰጥ ነው። ይፋ በተደረገው ነፃ የዓየር ሠዓት የተመዘገቡ 46 የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች በኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙ ይጠበቃል። በአጠቃላይ በምርጫ ካርድ መሪን መምረጥ ከሥልጣኔ ቁንጮዎች አንዱ ሆኖ ይነሳል። የመራጮች ምዝገባ ሂደትም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራርን እንዲያጠናክሩ ብሎም በካርዳቸው ይሁንታ የሚመራቸውን መምረጫ ቁልፍ ነው። ኢትዮጵያ በወሳኝ የምርጫ ወቅት ላይ ናትና፤ ለስኬታማነቱ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #የመራጮች_ምዝገባ #በኢዜአ_ዐይን
ተከፍሎ የማያልቅ የኢትዮጵያ እና ሕዝቧ ውለታ አለብን - የመናዊያን ፍልሰተኞች
Mar 19, 2026 2400
በዮሐንስ ደርበው ምድረ ቀደምቷ ሀገር ኢትዮጵያ ለተገፉ፣ ጥላ ከለላ ለሚሹ፣ ለተከዙና ለታረዙ የሀገራት ዜጎች መጠጊያ ናት። የኢትዮጵያን ቸርነትም ከተጠለሉባት እንግዶቿ በላይ ምሥክር የለም። የኢትዮጵያን ደጅ የረገጡ ሁሉ በቆይታቸው ለተደረገላቸው ሁሉ ‘ውለታችንን በምን እንክፈል’ ሲሉ ይደመጣሉ። ከአያሌ ሀገራት በመልከ ብዙ ቀውሶች ሳቢያ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሁሉ የቆሰሉ ልባቸው ታክሞ፣ ዕንባቸው ታብሶና ሕይወታቸው ታድሶ ኑራቸውን አደላድለዋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በዚህም ከአፍሪካም ሆነ ከተቀረው ክፍላተ ዓለም የጦርነትና ግጭት ጥላ ያጠላባቸውና ሰላምን የተጠሙ የቀጣናው ሀገራት ዜጎች ኢትዮጵያን ሲሹ ማየት የተለመደ ነው። የየመን ዜጎች ለዚህ ማሳያ ናቸው። ኢብቲሳም ኻሊድ እና መሰል የመናዊያን ከየመን የእርስ በርስ ግጭት በኋላ የኢትዮጵያን ደጅ ረግጠው ዛሬ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሚተርፍ የተድላ ኑሮ እየኖሩ ነው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረገችው ኢብቲሳም እንደምትለው፤ በየመን አለመረጋጋት በፈጠረው ጠባሳ እርሷና መሰሎቿ ለፍልሰት ተዳርገዋል። ለዚህ ደግሞ ምርጫቸው ኢትዮጵያ ሆነች። ወደ ኢትዮጵያም መጥተው የሀገሬው ፊት ሳይኮሰኩሳቸው በፍቅር እንደተቀበሏቸው ትናገራለች። በዚህም ዛሬ የመናዊያን ተስፋቸው ለምልሞ፣ ሕይወታቸው ሠምሮ ኢትዮጵያን እንደ እናት ቆጥረው እየኖሩ ስለመሆኑ ትናገራለች። ከ11 ዓመታት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የመጣችው ኢብቲሳም፤ በወቅቱ ቀኑ እንደጨለመባት ታወሳለች። ሰው ከቤቱ፣ ከወገኑ…ከሀገሩ ወጥቶ ወዴት ይሄዳል? በወቅቱ የነበረውን ጭንቀት ማየልም ታስታውሳለች። አሁን ግን ስለ ኢትዮጵያ እና ሕዝቧ በጎነት ዐውርታ አትጠግብም። “አሁን ፍልሰተኛ አይደለሁም፤ ያለሁት በሁለተኛዋ ሀገሬ ኢትዮጵያ ነውና” ትላለች። እንዲህ ባለው የረመዳን ወቅት ደግሞ የፍልሰተኞች ሁሉ ሰብሳቢ ናት። “ሁሉም ከእነ ቤተሰቡ ወደ ቤቷ እየመጣ ያፈጥራል። በዚህም በፍልሰት እንደመጡ ሳይሆን ቤተሰባዊነት ይሰማቸዋል። ከየመን፣ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ኤርትራ፣ አፍጋኒስታን፣ ኮንጎሊዝ (DRC) ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሁሉ ሰብሰብ ብለው የኢፍጣር መርሐ-ግብርን እንደሚያከናውኑም ታነሳለች። በዚህ ላይ ኢትዮጵያውያን ብርታት ናቸው ትላለች፤ ሁሌም ‘አይዟችሁ፣ በርቱ፣ ነገ ጥሩ ይሆናል’ እያሉ ያበረቱናል፤ ክብርና ፍቅር ይሰጡናል ስትልም ታስረዳለች። የኢትዮጵያንና ሕዝቧን ውለታ እንዴት መክፈል ይቻላል? ኢትዮጵያን ሀገራችን ብለን ነው እየጠራን ያለነው። እንደ እንግዳ እንደ ፍልሰተኛ እራሳችንን አናስብም፤ እንደሀገሬው አንዱ እንጅ፤ የምትለው ኢብቲሳም፤ ኢትዮጵያን እንዴት ብዬ ነው የምገልጻት? እናትን መግለጽ ይቻላል? እናትን መግለጽ ከተቻለ ኢትዮጵያን በዚያ ልክ መግለጽ ይቻል ይሆናል፤ እኔ ግን አይቻለኝም በማለት ትናገራለች። “የዛሬ 11 ዓመት ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት፤ የሰው ፊት አልገረፈኝም፤ ፊቱን ያዞረብኝም የለም። ኢትዮጵያውያን ደግ፣ ቅንና ደስ የምትሉ ሕዝቦች ናችሁ” ስትል ስሜቷን ትገልጻለች። ኢትዮጵያ እንደ ኒውዮርክ እያደገች ነው፤ እኛ ከመጣን በኋላ እንኳን በርካታ ለውጦች ዕያየን ነው ስትልም የኢትዮጵያን የለውጥ ሂደት አንስታለች። ለአብነትም ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በርካታ ነገሮች መስተካከላቸውን በመጠቆም፤ ለዚህም የኢትዮጵያን መንግሥት እናመሠግናለን ብላለች። ከፍልሰተኞች ጋር በተያያዘ በርካታ ሕጎች በመሻሻላቸው፤ ዛሬ በራሴ ስም ንግድ ፈቃድ አውጥቼ እየሠራሁ ነው፤ በጨረታዎችም እወዳደራለሁ፤ የበጎ አድራጎት ማኅበር መመሥረትና መምራት ችያለሁ። እነዚህ ሁሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ያመጣቸው ለውጦች ናቸው ብላለች። በምድረ ኢትዮጵያ ያለን ሁሉ ለኢትዮጵያ ዕድገት እንተባበር ስትልም ጥሪ አቅርባለች። ህልማችን ከኢትዮጵያውያን ጎን ሆነን ኢትዮጵያን በማሳደግ ጥረት በንቃት መሳተፍ ነው፤ የኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ውለታ መመለስ አለብን ስትልም ትናገራለች። በኢብቲሳም ኻሊድ ቤት በተዘጋጀ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይ የተሳተፈው አነስ አንዋር ለኢዜአ እንዳለው፤ ኢትዮጵያ በሯን ከፍታ አስጠልላዋለች። ከተለያዩ ሀገራት ብንመጣም ሰብሰብ ብለን ስናፈጥር፤ ማኅበራዊና ቤተሰባዊነታችን ይጠናክራል ብሏል። ብዙ ፈተናዎችን ዐይተናል፤ አልፈናቸው እዚህ ደርሰናል የሚለው አነስ፤ “ኢትዮጵያዊነት መልካምነት ነው” ሕዝቡ በክብር ነው የተቀበለን፤ ከምሥጋና ውጭ ምን ማለት እንችላለን? አመሥጋኞች ነን ሲል ገልጿል። እየተማርኩ ነው፤ ትምህርቴን አጠናቅቄ በሙያዬ በመሠማራት ኢትዮጵያን ማገዝ እፈልጋለሁ ብሏል። ራኪያ አሊ አብዱረዛቅ በበኩሏ በፈረንጆቹ 2011 ወደ ኢትዮጵያ መምጣቷን ታወሳለች። ትምህርቷንም ተከታትላ መመረቋን ገልጻ፤ ቤተሰብ አፍርታ ሁለት ልጆችንም ወልዳ እየኖረች ነው። ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሀገሬ ናት፤ ሰላም አላት፤ ሕዝቡም ሰው አክባሪ ነው። ለኢትዮጵያ የተሻለ ልማት ደግሞ መተባበር ወሳኝ ስለሆነ ለዚሁ እንትጋ ስትል መልዕክቷን አስተላልፋለች። #ፍልሰተኞች #ኢዜአ