ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በመደመር መንግስት እሳቤ የሀገርን የብልፅግና ጉዞ ለማሳካት እንሰራለን - አመራሮች
Dec 11, 2025 0
ሰቆጣ፣ ገንዳ ውሃ፣ ደብረ ብርሃን፣ ወልዲያ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በመደመር መንግስት እሳቤ የአካባቢን ፀጋ በማልማት የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ የአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢ አመራሮች ገለፁ። ‘’በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ’’ በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና የወሰዱ አመራሮች የማጠቃለያ ፕሮግራምና የልማት ስራዎች ጉብኝት ተካሄዷል። በዋግህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ሰቆጣ ከተማ ስልጠና ተሳታፊዎች መካከል አቶ አሻግሬ ደሳለኝ እና አቶ ታረቀ አለሙ እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት እሳቤ በህብረ ብሄራዊ መርህ ለሀገር ግንባታ መትጋት ነው።   የግብርናውን ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት የመላቀቅ ርዕይን ለማሳካት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ አክለዋል። ሌላዋ የስልጠናው ተሳታፊ ወይዘሮ ፀገነት ደምሴ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው ባገኙት እውቀት ህብረተሰቡ የተፋጠነ አገልግሎት እንዲያገኝ ሚናቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።   በተመሳሳይ በዞኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር የሀገሪቱን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥኑ ናቸው ያሉት ደግሞ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውኃና አካባቢው ያሉ የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሰልጣኞች ናቸው። የጉብኝቱ ተሳታፊ አቤሴሎም ጌታቸው እንዳሉት፤ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነውን አካባቢ ለአልሚዎች ይበልጥ ክፍት እንዲሆን የአመራርነት ሚናቸውን እንደሚወጡም አክለዋል።   ዮናስ ሞላልኝ እና አቶ አስማማው አለባቸው በበኩላቸው፤ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ሀብትን የማመቻቸት ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። መንግስት ያስቀመጣቸውን እድገት ተኮር ኢንሼቲቮች አሟጦ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ እንዳሉት፤ አመራሩ በጉብኝቱ የተመለከቷቸውን የልማት ተግባራት እንደየአካባቢያቸው ነባራዊ ሁኔታ ማስፋትና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢንዱስትሪ ዘርፉን በማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንን የገለፁት ደግሞ የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ደምሰው መንበሩ ናቸው። ባለፉት አምስት ወራት 32 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 211 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል። የጉብኝቱ ተሳታፊ አቶ ጥላየ ገብርየ እንዳሉት፤ ስልጠናውና በጉብኝቱ ሀገሪቱን ያለችበትን የእድገት ደረጃ ለመገንዘብ ያስቻለ ነው። ስልጠናው ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ኤልሳቤት ሀይለመስቀል ናቸው። የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው የተገኘውን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አገርን የመገንባትና የማዘመን ስራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከተማችንን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ሃብቶችን ማልማት ላይ ጠንክሮ ለመስራት የቤት ስራ የሰጠ ነው ብለዋል። በከተማ ግብርና፣ በወንዝ ዳርቻ ልማት፣ በሌማት ትሩፋትና በስራ እድል ፈጠራ የመደመር መንግስት ዕሳቤን የማሳኪያ ቁልፍ ስራዎች እንደሆኑም ገልጸዋል።
አመራሩ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል
Dec 11, 2025 13
ደሴ/ባሕርዳር፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፡-በተደመረ አቅምና እውቀት አመራሩ ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ተናገሩ። "የመደመር መንግስት እይታ፣የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በደሴና ባሕርዳር ለመካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።   በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ፤ በየደረጃው ያለው አመራር ለልማት ከመትጋት ባለፈ በቀናኢነት ህዝብን ለማገልገል የላቀ ዝግጁነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት ጭምር የተሟላ ስብእና በመላበስ ለችግሮች መፍትሄ መሻት፣ለሰላምና ልማት በጋራ መትጋት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን ግንዛቤ በመሰነቅ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል መዘጋጀት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የክልሉ መንግስት ከምንም በላይ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን፣ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሃብትና ጸጋዎችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የማድረግ የተቀናጀ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል።   ከስልጠናው ታሳትፊዎች መካከል ወይዘሮ ሶፊና አደም እና አቶ ኡመር አሰፋ፤ ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት ተግባር ላይ በማዋል ውጤት ለማምጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በባሕርዳር ከተማ የማጠቃለያ መድረክ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን፤ ‎በግብርና፣በኢንዱስትሪ፣ በከተሞች መሰረተ ልማትና በቱሪዝም ብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት ዘርፎች ላይ የተሰጡ ስልጠናዎችን በተቀናጀ መልኩ በተግባር መግለጥ ይገባል ብለዋል።   የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰፋ ጥላሁን፤ ‎የልማት እቅዶችን ማሳካት የሚቻለው በትብብር በመስራት በመሆኑ በዚሁ ልክ አመራሩ ዝግጁ ሆኖ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊ አመራሮችም በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።
በአማራ እና አፋር ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች የልማት ትስስሮችን ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Dec 11, 2025 13
ደሴ፤ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በአማራ እና አፋር ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች የሰላም ግንባታና የልማት ትስስሮችን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። የሁለቱ ክልሎች የሰላምና ፀጥታ አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በአዋሳኝ አካባቢዎች በዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች ዙሪያ በኮምቦልቻ ከተማ ውይይት አድርገዋል። የአማራ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር)፥የክልሎቹ አጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች ጠንካራ አብሮነት ያላቸው መሆኑንና የሚጋሯቸው በርካታ እሴቶች እንዳሏቸው አንስተዋል።   እነዚህን እሴቶች በማጎልበት የሰላም ግንባታና የልማት ትስስሮችን ይበልጥ ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አጽኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም በሁሉቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሰላም ግንባታን የማጎልበትና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል። በተለይም የመሰረተ ልማትና የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማጠናከር እንዲሁም ሰላምን በማጽናት ረገድ በቀጣይ የተቀናጀ ጥረት እናደርጋለን ሲሉ ተናግረዋል። የአፋር ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ኮሚሽነር አህመድ ሁመድ በበኩላቸው፥ በሁሉቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በሰላምና የልማት ስራዎች ጉዳይ ይበልጥ ተቀራርበን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።   በመሰረተ ልማትና የገበያ ትስስር እንዲሁም በሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ስለመሆኑም አንስተዋል። በመሆኑም እነዚህን አጠናክሮ በመቀጠል የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበልጥ ተቀናጅተን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። ግጭት ሰባቂዎችን በጋራ መመከትና የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ይገባል ያሉት ደግሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ቸሩጌታ ገነነ፤ በኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   ይሁን እንጂ በተለያዩ አካባቢዎች ከልማት ይልቅ ግጭትና አለመረጋጋት እንዲፈጠር የሚጥሩ የጥፋት ተልእኮ ያነገቡ አካላት ስለመኖራቸው አንስተው ሰላምን ማጽናትና ለልማት መትጋት የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል። በመሆኑም በአፋርና አማራ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አጽዕኖት ሰጥተዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምስራቅ እዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አሰፋ ቸኮል፤ በሁሉም አካባቢዎች ዘላቂ ሰላምን ማስጠበቅና የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት እውን ማድረግ የጋራ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል። በተለይም በአካባቢው በስፋት የሚስተዋለውን ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከል፣ የመሳሪያና ሌሎችም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን በጥብቅ መከታተልና በጋራ መከላከል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በመድረኩ የፌዴራል፣ የሁለቱ ክልልች እንዲሁም የዞንና የወረዳ አመራሮች፣ የፀጥታ አባላት እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች ነው
Dec 11, 2025 20
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ። በአፍሪካ ሕብረት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች ጉባዔ ተጠናቋል። ጉባኤው አህጉሪቱ እያጋጠሙ የሚገኙትን ሽብርተኝነት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና ሌሎች የደኅንነት ችግሮችን በተባበረ ክንድ መፍታት ላይ ያለመ ነው። መሪዎቹ የአፍሪካን የሠላምና የፀጥታ ችግሮች የሌላ አካል ጣልቃ ገብነት ሳይስፈልግ እንዴት በራስ አቅም ብቻ መፍታት እንደሚቻል በዝርዝር ተወያይተዋል።   ለቀናት በልዩ ልዩ አፍሪካዊ ጉዳዮች ሲመክር የቆዬው የመከላከያ መሪዎች ጉባኤ ቀጠናዊ ሠላምና መረጋጋትን ማስፈን፣ በሶማሊያ አልሸባብን ማስወገድ፣ በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ለሠላም ማስከበር ተልዕኮ የፋይናንስ ድጋፍ በሚሉትና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ የመፍትሔ አቅጣጫ አስቀምጧል። ኢትዮጵያ ለሠላም ባላት ጠንካራ አቋምና ተምሣሌትነት ተመርጣ ጉባኤውን ለተከታታይ ዓመታት እያስተናገደች መሆኗን ያነሱት የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት እየሠራች እንደምትገኝም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ የሚስተዋል ችግሮችን በፍጥነት የሚፈታ የተባበረ የአፍሪካ የተጠንቀቅ ኃይል አስፈላጊነት ላይ መወያየቱን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ለአህጉሪቱ ያላት አስተዋፅኦ የተንፀባረቀበት ጉባኤ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለሶማሊያ ሕዝብ ሠላም ላበረከተው አስተዋፅኦ በስብሰባው ከፍተኛ እውቅና መሰጠቱን ያወሱት በመከላከያ የዓለም አቀፍና የጎረቤት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ሰብስቤ ዱባ በቀጣይም የአህጉሪቱን ችግሮች በትብብር እየፈቱ ለመሄድ ከስምምነት መደረሱን ገልፀዋል።   ሁሉም የአፍሪካ አባል ሀገራት የሚሳተፉበት የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች የሠላምና ደኅንነት ጉባኤ በየዓመቱ የሚካሄድ መሁኑም ተመላክትል። 17ኛውን የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች ስብሰባ እና 20ኛው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሞችና የደህንነት ኃላፊዎች ስብሰባ ከህዳር 29 እስከ ታህሳስ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መካሄዱን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል።
የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ ነው
Dec 11, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማጠናከር የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የጤና ሚኒስቴር የእናቶች፣ የህፃናትና ወጣቶች ጤና አጠባበቅ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ አካሒዷል።   የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች። በተለይም የእናቶችና ህፃናት ጤና አጠባበቅ እና ተደራሽነት ላይ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል። እነዚህ ስኬቶች በመንግስት ቁርጠኝነት እና በአጋር አካላት ያልተቋረጠ ድጋፍ የተገኙ መሆናቸውን ገልፀዋል።   ኢትዮጵያ የእናቶችና ህፃናት ጤና በሁሉም የጤና ተቋማት በተሟላ መልኩ መስጠት የሚያስችል ጥረት እያደረገች ነው ያሉት ሚኒስትሯ፥ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማጠናከር የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የእናቶችና የህጻናት ሞትን ለመቀነስ ያስቀመጠችውን ግብ ለማሳካት ዕቅድ ነድፋ እየሰራች መሆኑን አንስተዋል።   ለዚህ ሥራ ይበልጥ መጠናከር የሚውል የሀብት ማሰባሰብ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው እስካሁንም ከአጋር አካላት ከ160 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሃብት መሰብሰቡን ነው ያነሱት። ይህ ሃብት ከዚህ ዓመት ጀምሮ ለሦስት ዓመታት ጥቅም ላይ እንደሚውል በመጥቀስ የሀብት ማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የተሰበሰበው ሃብት ለህክምና ቁሳቁስና ግብዓት፣ ለጤና ተቋማት ግንባታ፣ ለጤና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታና መሰል ስራዎች እንደሚውል ሚኒስትር ዴኤታው አክለዋል።   በኢትዮጵያ የኔዘርላንድ አምባሳደርና የአጋር አካላት የሃብት ማሰባሰብ አስተባባሪ ክርስቲን ፒሬን፥ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያስመዘገበች ያለው ውጤት የሚበረታታ ነው ብለዋል። በተለይም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ሁሉም አጋር አካላት የሚከናወኑ ተግባራትን ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላቸው ጠቁመው መሰል የሃብት ማሰባሰብና የድጋፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የሚታይ
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች ነው
Dec 11, 2025 20
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ። በአፍሪካ ሕብረት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች ጉባዔ ተጠናቋል። ጉባኤው አህጉሪቱ እያጋጠሙ የሚገኙትን ሽብርተኝነት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና ሌሎች የደኅንነት ችግሮችን በተባበረ ክንድ መፍታት ላይ ያለመ ነው። መሪዎቹ የአፍሪካን የሠላምና የፀጥታ ችግሮች የሌላ አካል ጣልቃ ገብነት ሳይስፈልግ እንዴት በራስ አቅም ብቻ መፍታት እንደሚቻል በዝርዝር ተወያይተዋል።   ለቀናት በልዩ ልዩ አፍሪካዊ ጉዳዮች ሲመክር የቆዬው የመከላከያ መሪዎች ጉባኤ ቀጠናዊ ሠላምና መረጋጋትን ማስፈን፣ በሶማሊያ አልሸባብን ማስወገድ፣ በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ለሠላም ማስከበር ተልዕኮ የፋይናንስ ድጋፍ በሚሉትና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ የመፍትሔ አቅጣጫ አስቀምጧል። ኢትዮጵያ ለሠላም ባላት ጠንካራ አቋምና ተምሣሌትነት ተመርጣ ጉባኤውን ለተከታታይ ዓመታት እያስተናገደች መሆኗን ያነሱት የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት እየሠራች እንደምትገኝም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ የሚስተዋል ችግሮችን በፍጥነት የሚፈታ የተባበረ የአፍሪካ የተጠንቀቅ ኃይል አስፈላጊነት ላይ መወያየቱን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ለአህጉሪቱ ያላት አስተዋፅኦ የተንፀባረቀበት ጉባኤ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለሶማሊያ ሕዝብ ሠላም ላበረከተው አስተዋፅኦ በስብሰባው ከፍተኛ እውቅና መሰጠቱን ያወሱት በመከላከያ የዓለም አቀፍና የጎረቤት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ሰብስቤ ዱባ በቀጣይም የአህጉሪቱን ችግሮች በትብብር እየፈቱ ለመሄድ ከስምምነት መደረሱን ገልፀዋል።   ሁሉም የአፍሪካ አባል ሀገራት የሚሳተፉበት የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች የሠላምና ደኅንነት ጉባኤ በየዓመቱ የሚካሄድ መሁኑም ተመላክትል። 17ኛውን የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች ስብሰባ እና 20ኛው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሞችና የደህንነት ኃላፊዎች ስብሰባ ከህዳር 29 እስከ ታህሳስ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መካሄዱን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል።
የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ ነው
Dec 11, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማጠናከር የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የጤና ሚኒስቴር የእናቶች፣ የህፃናትና ወጣቶች ጤና አጠባበቅ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ አካሒዷል።   የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች። በተለይም የእናቶችና ህፃናት ጤና አጠባበቅ እና ተደራሽነት ላይ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል። እነዚህ ስኬቶች በመንግስት ቁርጠኝነት እና በአጋር አካላት ያልተቋረጠ ድጋፍ የተገኙ መሆናቸውን ገልፀዋል።   ኢትዮጵያ የእናቶችና ህፃናት ጤና በሁሉም የጤና ተቋማት በተሟላ መልኩ መስጠት የሚያስችል ጥረት እያደረገች ነው ያሉት ሚኒስትሯ፥ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማጠናከር የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የእናቶችና የህጻናት ሞትን ለመቀነስ ያስቀመጠችውን ግብ ለማሳካት ዕቅድ ነድፋ እየሰራች መሆኑን አንስተዋል።   ለዚህ ሥራ ይበልጥ መጠናከር የሚውል የሀብት ማሰባሰብ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው እስካሁንም ከአጋር አካላት ከ160 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሃብት መሰብሰቡን ነው ያነሱት። ይህ ሃብት ከዚህ ዓመት ጀምሮ ለሦስት ዓመታት ጥቅም ላይ እንደሚውል በመጥቀስ የሀብት ማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የተሰበሰበው ሃብት ለህክምና ቁሳቁስና ግብዓት፣ ለጤና ተቋማት ግንባታ፣ ለጤና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታና መሰል ስራዎች እንደሚውል ሚኒስትር ዴኤታው አክለዋል።   በኢትዮጵያ የኔዘርላንድ አምባሳደርና የአጋር አካላት የሃብት ማሰባሰብ አስተባባሪ ክርስቲን ፒሬን፥ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያስመዘገበች ያለው ውጤት የሚበረታታ ነው ብለዋል። በተለይም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ሁሉም አጋር አካላት የሚከናወኑ ተግባራትን ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላቸው ጠቁመው መሰል የሃብት ማሰባሰብና የድጋፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
አውደ ጥናቱ ለኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ኃይል ልማት ቀጣይ ስራዎች መደላድል የሚሆን ግንዛቤ ተፈጥሮበታል
Dec 11, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦አውደ ጥናቱ ለኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ኃይል ልማት ቀጣይ ስራዎች መደላድል የሚሆን ግንዛቤ የተፈጠረበት መሆኑን የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ገለጸ። የመጀመሪያው ብሔራዊ የኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር ሚና እና ኃላፊነት የተቋም ትግበራ አውደ ጥናት ምክክር መድረክ ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሽፈራው ተሊላ በዚሁ ወቅት፥ የኒውክሊየር ኃይል ለኢነርጂ፣ ለግብርና፣ ለጤና እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገለጸዋል። የዚህ ኃይል አጠቃቀም በዓለም አቀፍ ሕግ የሚመራ መሆኑን ገልጸው ሀገራት ሊከተሏቸወ የሚገቡ ቅደም ተከተሎች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በአውደ ጥናቱ በሀገር ውስጥ ያሉ ባለድርሻ አካላት እና የሚመለከታቸው ሌሎች ተቋማት መሳተፋቸውንና ግንዛቤ መፈጠሩን ተናግረዋል። የኒውክሊየር ፕሮግራሙ ሀገራዊ ፕሮጀከት በመሆኑ ህብረተሰቡ ለስኬቱ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ ማስቻል ላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። በአውደ ጥናቱ በዓለም አቀፍ የሕግ ማእቀፎች እና ሊከናወኑ በሚገባቸው ስራዎች ላይ ውይይት መደረጉንም አመላክተዋል። የተቋማት አቅም እና የሰው ኃይል ግንባታ ሌላኛው በአውደ ጥናቱ በስፋት የተዳሰሰ መሆኑን ጠቁመዋል።   አውደጥናቱ በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ልማት ቀጣይ ስራዎች መደላድል የሚሆን ግንዛቤ የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል። በአውደ ጥናቱ ከተሳተፉት መካከል የውመን ኢን ኒውክሊየር ኢትዮጵያ ፕሬዝደንት አበባ ጌጡ፤ አውደ ጥናቱ በቂ ግንዛቤ ያገኙበት መሆኑን ገልጸዋል።   በተለይም የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ባስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ላይ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ነው የገለጹት። በቀጣይም በፕሮግራሙ ላይ የሴቶች አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንዲሆን በስልጠና እንዲሁም በተለያዩ አውደ ጥናቶች የማብቃት ስራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። በአውደ ጥናቱ ጥልቅ እውቀት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ በኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን የጨረራና ኒውክሊየር ቴክኖሎጂ የማሳወቅ እና ፈቃድ አሰጣጥ መሪ ስራ አስፈጻሚ ስሩር ከድር ናቸው። ተጨማሪ እውቀት በመፍጠር በዘርፉ የተሰማሩትን ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳ መሆኑን ተናግረዋል።
በመዲናዋ የህዝብ እርካታን የሚያሳድጉ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 11, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የህዝብ እርካታን የሚያሳድጉ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥን የሚያሳልጡ ስማርት የወረዳ አስተዳደር ህንጻዎችን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።   ለምረቃ የበቁት የአስተዳደር ህንጻዎች በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ፣ በላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 እና ወረዳ 1 የሚገኙ ህንጻዎች ናቸው። ህንጻዎቹ የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በተናበበ እና በተሳለጠ መልኩ ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ ሲሆን የአገልግሎት መስጫ ቢሮዎች ፣የመሰብሰቢያ አዳራሾችና የመኪና ማቆሚያዎች የተሟሉላቸው ናቸው፡፡ ህንጻዎቹ የህጻናት ማቆያ፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን ጨምሮ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ የሆኑ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውም በዚሁ መርሐ ግብር ላይ ተመላክቷል፡፡   ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ እያደገ ለመጣው የህዝብ ፍላጎት ተመጣጣኝ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ዘመኑን የዋጁ አገልግሎቶች ተደራሽ ማድረግ ጊዜው የሚጠይቀው ነው፡፡   የከተማ አስተዳደሩ ቀልጣፋና የተናበበ አገልግሎት ለመስጠት የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል ። ዛሬ በሶስት ቦታዎች ላይ የተመረቁት ስማርት አገልግሎት መስጫ ህንጻዎች የዚህ ጥረት ማሳያ ናቸውም ብለዋል፡፡ አገልግሎት አሳጣጡ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን ከግንባታ ባሻገር ለሰው ሃይልም ሰፊ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡   አገልግሎት ሰጪዎች በክህሎት እና በአመለካከት የዳበሩ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ የመዲናዋ አመራሮች የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ዛሬ በይፋ የተመረቁት ስማርት አገልግሎት መስጫ ህንጻዎችን ደረጃ በደረጃ በሌሎች ክፍለ ከተሞችም የማስፋፋት ተግባራት እንደሚከናወን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የግልፅነት መርህ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደትን እያፋጠነ ነው
Dec 11, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የግልፅነት መርህ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችውን ሂደት እያፋጠነ መሆኑን የዓለም ንግድ ድርጅት አክሴሽን ዲቪዥን ዳይሬክተር ማይካ ኦሺካዋ ገለጹ፡፡ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር ሂደት እና በተከናወኑ ስራዎች ላይ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ለመፍጠር "ኢትዮጵያን በንግድ በማስተሳሰር፤ ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው ፎረም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል፡፡   የዓለም ንግድ ድርጅት አክሴሽን ዲቪዥን ዳይሬክተር ማይካ ኦሺካዋ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን የተቀመጡ መስፈርቶችን በፍጥነት እያካሄደች ትገኛለች ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የአባልነት ሂደት 22 ዓመታትን ማስቆጠሩን አስታውሰው አሁን ላይ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት አመርቂ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን ቀጣይነት ያለው ተሳትፎ እያከናወነች መሆኑን ጠቅሰው በቴክኒክ ደረጃ ሙሉ ለሙሉ የተጠናከረ የድርድር ሂደት እያካሄደች እንደምትገኝ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በስድስተኛው የድርድር ሂደት ለቀረቡላት ሁሉም ጥያቄዎች በቂ ምላሽ መስጠቷ የሀገር ውስጥ የፖሊሲ ጥንካሬዎችንና ውሳኔዎችን ያመላክታል ብለዋል፡፡ በድርድር ሂደቱ ሙሉ በሙሉ በሰነድ የተደገፈ ግብዓት ማቅረቧ ለገበያ ተደራሽነት ወሳኝ መሠረት ለመጣል እንደሚያስችላት ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዕቃዎችና አገልግሎቶች ዙሪያ ያቀረበችው የተመጣጠነ ዋጋ ጠንካራ እና ተዓማኒነት ያለው መሆኑን አስር አባል ሀገራት ማረጋገጣቸውን አስታውቀዋል፡፡ በዚህም አባል ሀገራቱ በፍጥነት ወደ ዝርዝር የቴክኒክ ድርድር ለመግባት ፍላጎት እንዳላቸው ማሳየታቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከ1 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት መቻሏን ጠቁመው ለዓለም የንግድ ድርጅት አባላት ያቀረበቻቸው የሕግ ሰነዶች 400 መድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡   ይህም በሌሎች ሀገራት የድርድር ሂደት ከታዩት እጅግ ከፍተኛው ቁጥር በመሆኑ ለዓለም ንግድ ድርጅት የግልጽነት መርህ ምሳሌ ሆናለች ብለዋል። ከድርድር ቡድኑ ሚና ባሻገርም የኢትዮጵያ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርም ለአባልነት ሂደቱ መፋጠን ወሳኝ አበርክቶ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ይህም የኢትዮጵያን የአባልነት ጉዞ ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ገልጸው ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ ጋር የሚጣጣም ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በመደመር መንግስት እሳቤ የሀገርን የብልፅግና ጉዞ ለማሳካት እንሰራለን - አመራሮች
Dec 11, 2025 0
ሰቆጣ፣ ገንዳ ውሃ፣ ደብረ ብርሃን፣ ወልዲያ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በመደመር መንግስት እሳቤ የአካባቢን ፀጋ በማልማት የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ የአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢ አመራሮች ገለፁ። ‘’በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ’’ በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና የወሰዱ አመራሮች የማጠቃለያ ፕሮግራምና የልማት ስራዎች ጉብኝት ተካሄዷል። በዋግህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ሰቆጣ ከተማ ስልጠና ተሳታፊዎች መካከል አቶ አሻግሬ ደሳለኝ እና አቶ ታረቀ አለሙ እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት እሳቤ በህብረ ብሄራዊ መርህ ለሀገር ግንባታ መትጋት ነው።   የግብርናውን ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት የመላቀቅ ርዕይን ለማሳካት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ አክለዋል። ሌላዋ የስልጠናው ተሳታፊ ወይዘሮ ፀገነት ደምሴ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው ባገኙት እውቀት ህብረተሰቡ የተፋጠነ አገልግሎት እንዲያገኝ ሚናቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።   በተመሳሳይ በዞኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር የሀገሪቱን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥኑ ናቸው ያሉት ደግሞ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውኃና አካባቢው ያሉ የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሰልጣኞች ናቸው። የጉብኝቱ ተሳታፊ አቤሴሎም ጌታቸው እንዳሉት፤ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነውን አካባቢ ለአልሚዎች ይበልጥ ክፍት እንዲሆን የአመራርነት ሚናቸውን እንደሚወጡም አክለዋል።   ዮናስ ሞላልኝ እና አቶ አስማማው አለባቸው በበኩላቸው፤ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ሀብትን የማመቻቸት ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። መንግስት ያስቀመጣቸውን እድገት ተኮር ኢንሼቲቮች አሟጦ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ እንዳሉት፤ አመራሩ በጉብኝቱ የተመለከቷቸውን የልማት ተግባራት እንደየአካባቢያቸው ነባራዊ ሁኔታ ማስፋትና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢንዱስትሪ ዘርፉን በማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንን የገለፁት ደግሞ የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ደምሰው መንበሩ ናቸው። ባለፉት አምስት ወራት 32 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 211 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል። የጉብኝቱ ተሳታፊ አቶ ጥላየ ገብርየ እንዳሉት፤ ስልጠናውና በጉብኝቱ ሀገሪቱን ያለችበትን የእድገት ደረጃ ለመገንዘብ ያስቻለ ነው። ስልጠናው ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ኤልሳቤት ሀይለመስቀል ናቸው። የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው የተገኘውን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አገርን የመገንባትና የማዘመን ስራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከተማችንን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ሃብቶችን ማልማት ላይ ጠንክሮ ለመስራት የቤት ስራ የሰጠ ነው ብለዋል። በከተማ ግብርና፣ በወንዝ ዳርቻ ልማት፣ በሌማት ትሩፋትና በስራ እድል ፈጠራ የመደመር መንግስት ዕሳቤን የማሳኪያ ቁልፍ ስራዎች እንደሆኑም ገልጸዋል።
አመራሩ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል
Dec 11, 2025 13
ደሴ/ባሕርዳር፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፡-በተደመረ አቅምና እውቀት አመራሩ ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ተናገሩ። "የመደመር መንግስት እይታ፣የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በደሴና ባሕርዳር ለመካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።   በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ፤ በየደረጃው ያለው አመራር ለልማት ከመትጋት ባለፈ በቀናኢነት ህዝብን ለማገልገል የላቀ ዝግጁነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት ጭምር የተሟላ ስብእና በመላበስ ለችግሮች መፍትሄ መሻት፣ለሰላምና ልማት በጋራ መትጋት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን ግንዛቤ በመሰነቅ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል መዘጋጀት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የክልሉ መንግስት ከምንም በላይ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን፣ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሃብትና ጸጋዎችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የማድረግ የተቀናጀ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል።   ከስልጠናው ታሳትፊዎች መካከል ወይዘሮ ሶፊና አደም እና አቶ ኡመር አሰፋ፤ ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት ተግባር ላይ በማዋል ውጤት ለማምጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በባሕርዳር ከተማ የማጠቃለያ መድረክ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን፤ ‎በግብርና፣በኢንዱስትሪ፣ በከተሞች መሰረተ ልማትና በቱሪዝም ብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት ዘርፎች ላይ የተሰጡ ስልጠናዎችን በተቀናጀ መልኩ በተግባር መግለጥ ይገባል ብለዋል።   የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰፋ ጥላሁን፤ ‎የልማት እቅዶችን ማሳካት የሚቻለው በትብብር በመስራት በመሆኑ በዚሁ ልክ አመራሩ ዝግጁ ሆኖ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊ አመራሮችም በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።
በአማራ እና አፋር ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች የልማት ትስስሮችን ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Dec 11, 2025 13
ደሴ፤ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በአማራ እና አፋር ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች የሰላም ግንባታና የልማት ትስስሮችን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። የሁለቱ ክልሎች የሰላምና ፀጥታ አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በአዋሳኝ አካባቢዎች በዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች ዙሪያ በኮምቦልቻ ከተማ ውይይት አድርገዋል። የአማራ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር)፥የክልሎቹ አጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች ጠንካራ አብሮነት ያላቸው መሆኑንና የሚጋሯቸው በርካታ እሴቶች እንዳሏቸው አንስተዋል።   እነዚህን እሴቶች በማጎልበት የሰላም ግንባታና የልማት ትስስሮችን ይበልጥ ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አጽኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም በሁሉቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሰላም ግንባታን የማጎልበትና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል። በተለይም የመሰረተ ልማትና የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማጠናከር እንዲሁም ሰላምን በማጽናት ረገድ በቀጣይ የተቀናጀ ጥረት እናደርጋለን ሲሉ ተናግረዋል። የአፋር ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ኮሚሽነር አህመድ ሁመድ በበኩላቸው፥ በሁሉቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በሰላምና የልማት ስራዎች ጉዳይ ይበልጥ ተቀራርበን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።   በመሰረተ ልማትና የገበያ ትስስር እንዲሁም በሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ስለመሆኑም አንስተዋል። በመሆኑም እነዚህን አጠናክሮ በመቀጠል የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበልጥ ተቀናጅተን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። ግጭት ሰባቂዎችን በጋራ መመከትና የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ይገባል ያሉት ደግሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ቸሩጌታ ገነነ፤ በኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   ይሁን እንጂ በተለያዩ አካባቢዎች ከልማት ይልቅ ግጭትና አለመረጋጋት እንዲፈጠር የሚጥሩ የጥፋት ተልእኮ ያነገቡ አካላት ስለመኖራቸው አንስተው ሰላምን ማጽናትና ለልማት መትጋት የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል። በመሆኑም በአፋርና አማራ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አጽዕኖት ሰጥተዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምስራቅ እዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አሰፋ ቸኮል፤ በሁሉም አካባቢዎች ዘላቂ ሰላምን ማስጠበቅና የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት እውን ማድረግ የጋራ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል። በተለይም በአካባቢው በስፋት የሚስተዋለውን ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከል፣ የመሳሪያና ሌሎችም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን በጥብቅ መከታተልና በጋራ መከላከል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በመድረኩ የፌዴራል፣ የሁለቱ ክልልች እንዲሁም የዞንና የወረዳ አመራሮች፣ የፀጥታ አባላት እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች ነው
Dec 11, 2025 20
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ። በአፍሪካ ሕብረት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች ጉባዔ ተጠናቋል። ጉባኤው አህጉሪቱ እያጋጠሙ የሚገኙትን ሽብርተኝነት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና ሌሎች የደኅንነት ችግሮችን በተባበረ ክንድ መፍታት ላይ ያለመ ነው። መሪዎቹ የአፍሪካን የሠላምና የፀጥታ ችግሮች የሌላ አካል ጣልቃ ገብነት ሳይስፈልግ እንዴት በራስ አቅም ብቻ መፍታት እንደሚቻል በዝርዝር ተወያይተዋል።   ለቀናት በልዩ ልዩ አፍሪካዊ ጉዳዮች ሲመክር የቆዬው የመከላከያ መሪዎች ጉባኤ ቀጠናዊ ሠላምና መረጋጋትን ማስፈን፣ በሶማሊያ አልሸባብን ማስወገድ፣ በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ለሠላም ማስከበር ተልዕኮ የፋይናንስ ድጋፍ በሚሉትና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ የመፍትሔ አቅጣጫ አስቀምጧል። ኢትዮጵያ ለሠላም ባላት ጠንካራ አቋምና ተምሣሌትነት ተመርጣ ጉባኤውን ለተከታታይ ዓመታት እያስተናገደች መሆኗን ያነሱት የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት እየሠራች እንደምትገኝም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ የሚስተዋል ችግሮችን በፍጥነት የሚፈታ የተባበረ የአፍሪካ የተጠንቀቅ ኃይል አስፈላጊነት ላይ መወያየቱን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ለአህጉሪቱ ያላት አስተዋፅኦ የተንፀባረቀበት ጉባኤ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለሶማሊያ ሕዝብ ሠላም ላበረከተው አስተዋፅኦ በስብሰባው ከፍተኛ እውቅና መሰጠቱን ያወሱት በመከላከያ የዓለም አቀፍና የጎረቤት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ሰብስቤ ዱባ በቀጣይም የአህጉሪቱን ችግሮች በትብብር እየፈቱ ለመሄድ ከስምምነት መደረሱን ገልፀዋል።   ሁሉም የአፍሪካ አባል ሀገራት የሚሳተፉበት የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች የሠላምና ደኅንነት ጉባኤ በየዓመቱ የሚካሄድ መሁኑም ተመላክትል። 17ኛውን የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች ስብሰባ እና 20ኛው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሞችና የደህንነት ኃላፊዎች ስብሰባ ከህዳር 29 እስከ ታህሳስ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መካሄዱን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል።
የመደመር መንግስት እሳቤ ሀገር አሻጋሪ ራዕይ ያለው በመሆኑ ለተግባራዊነቱ እንተጋለን-አመራሮች 
Dec 11, 2025 86
ጎንደር ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፡- የመደመር መንግስት እሳቤ ሀገር አሻጋሪ ራዕይና ተልዕኮ ያለው በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ግንባር ቀደም በመሆን በቁርጠኝነት እንተጋለን ሲሉ የጎንደር ማዕከል ሰልጣኝ አመራሮች ተናገሩ። ከጎንደር ከተማ አስተዳደርና ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን የተውጣጡ አመራሮች በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል። ከሰልጣኝ አመራሮቹ ውስጥ አቶ ነጋ አሰፋ፤ የመደመር መንግስት እሳቤዎች ብዝሀ ኢኮኖሚን በመገንባት ለብልጽግና ጉዞ መሳካት ትልቅ የኢኮኖሚ ምሰሶ ነው ብለዋል።   መንግስት ለከተሞች ልማትና እድገት መፋጠን የጀመራቸው ተግባራት በከተሞች ድህነትና ስራ አጥነት ችግር በመፍታት በኩል ታላቅ ተስፋን የፈነጠቀ እርምጃ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ ሌላው ተሳታፊ አቶ ዋሲሁን ሞላ እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት እሳቤዎች በኢትዮጵያ ዘላቂና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገት እንዲመዘገብ የተቀመጠውን ግብ አመራሩ በቁርጠኝነት እንዲፈጽም ምቹ የፖለቲካ አውድ የሚፈጥር ነው፡፡ ስልጠናው የነበረብንን የአስተሳሰብና የእውቀት ክፍተቶች በመሙላት በቀጣይ ሀገር አሻጋሪ የሆነውን የመደመር መንግስት እሳቤዎች ከአካባቢያችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማዛመድ መተግበር እንድንችል አቅም ፈጥሮልናል ብለዋል፡፡ በቅርቡ የተፈረመው የዘላቂ ሰላም ስምምነት አዎንታዊ እርምጃ ከመሆኑም በላይ አመራሩና ሕዝቡ በቅንጅት እያከነወኑት ላለው የሰላም ግንባታ ተግባራት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡   የመደመር መንግስት እሳቤዎች ኢትዮጵያ ያሏትን እምቅ የልማት አቅሞችና የተፈጥሮ ሀብት ጸጋዎች እንድትጠቀም ምቹ ሀገር በቀል የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያመላከተ ነው ያሉት ደግሞ አቶ አበበ ጌጡ ናቸው፡፡ ስልጠናው የአመራሩን እሳቤዎችና እይታዎች በማሳደግ በተደመረ አቅም በመፍጠርና በመፍጠን መርህ የብልፅግና ጉዞው ስኬታማ እንዲሆን አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር እንደሆነ ጠቁመው ፤ ለተግባራዊነቱም ግንባር ቀደም በመሆን በቁርጠኝነት እንደሚተጉ ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ የተደረሰው የዘላቂ ሰላም ስምምነት መንግስት ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ጠቁመው፤ ሰላምን የማፅናቱ ተግባር እንዲሳካ በግንባር ቀደምትነት ጠንከረው እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡   በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች መልካም ተሞክሮ የሚቀሰምባቸው እንደሆኑ ሰልጣኝ አመራሮቹ ተናግረዋል፡፡ የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ስራም መንግስት ለታሪካዊ ቅርሶች ጥበቃ የሰጠው ትኩረት ማሳያ እንደሆነ አመልክተው፤ የከተማ ግብርና ስራዎችም የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ድርሻቸው የላቀ መሆኑን በምልከታው መገንዘባቸውን ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት፣ የከተማ ግብርና የቱሪዝም መዳረሻ ልማቶችንና ኢንዱስትሪዎችን እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በአካባቢው ያለውን አስተማማኝ ሰላም በማጽናት የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ በቅንጅት እየተሰራ ነው
Dec 11, 2025 83
ሐረር ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን አስተማማኝ ሰላም በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የምስራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ፍቃዱ ፀጋዬ ገለጹ። የምስራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች ክልሎች፣ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ ጥምር ግብረ ኃይል በሠላምና ፀጥታ ዙሪያ ውይይት አካሄደዋል።   የውይይቱ ዓላማም በዞኖች እና ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት የአካባቢውን ሠላም እና ፀጥታ የበለጠ አጠናክረው ለማስቀጠል ያለመ መሆኑ ታውቋል። የውይይት መድረኩን የመሩት የምስራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ፍቃዱ ፀጋዬ፤ በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን አስተማማኝ ሰላም በማዝለቅ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል። በተለይም አካባቢው ከፍተኛ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ የሚታይበትና አሸባሪዎች ሰላምን ለማናጋት የሚጥሩበት በመሆኑ የጸጥታ አካላት ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት ሌት ከቀን ለሰላም የሚሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።   የጸጥታ አካላት በቅንጅትና በትብብር የሰላም ዘብ ሆነው እየሰሩ መሆኑን አንስተው የሀገር መከላከያ ሰራዊትም ሰላምን በማጽናት የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የላቀ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የሐረሪ፣ በኦሮሚያ ክልል የምስራቅ እና የምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች፣ በሶማሌ ክልል የሲቲ እና የፋፈን ዞኖች፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና የማያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ አመራሮችና የፖሊስ ኮሚሽነሮች እንዲሁም የምስራቅ ዕዝ እና የፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በጫካ የሚንቀሳቀሱ አካላት የሀገርና ሕዝብን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ የሰላም አማራጭ ሊቀበሉ ይገባል - የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ከፍተኛ አመራሮች
Dec 11, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በጫካ የሚንቀሳቀሱ አካላት የሀገርና ሕዝብን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ የሰላም አማራጭ ሊቀበሉ እንደማገባ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ከፍተኛ አመራሮች አስታወቁ። የአማራ ሕዝብ በውክልና ጦርነት እንዲቆይ የሚሹ የጥፋት ተልዕኮዎችን በመተው ትክክለኛውን የሰላም ስምምነት አማራጭ መቀበላቸውንም ገልጸዋል። በአማራ ክልል መንግስትና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የተፈረመውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።   በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ምክትል የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊና የወሎ ቤተ-አማራ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ እያሡ አበራ፥ የአማራን ህዝብ ጥያቄ በትጥቅ ትግል እናስከብራለን በሚል በጫካ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በአማራ ክልል መንግስትና በሕዝባዊ ድርጅቱ የተፈረመው የሰላም ስምምነትም የአማራን ሕዝብ ክብርና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ባከበረ መንገድ የተፈጸመ መሆኑን ተናግረዋል። በተፈረመው የሰላም ስምምነትም በዘፈቀደ የተመራ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ዕውቅና ባለው መንገድ የተፈጸመ መሆኑንም አንስቷል። የአማራ ሕዝብ ከዚህ በላይ ጦርነትን የመሸከም አቅም የለውም፥ ሌሎች በጫካ የሚንቀሳቀሱ አካላትም የሕዝብና የሀገርን ጥቅምና ክብር በሚያስከብር አግባብ የሰላም አማራጭን መቀበል አለባቸው ብለዋል። በዚህም ለሕዝብ የሚበጅ ትክክለኛ የንግግር ውሳኔን በማሳለፍ የሰላም አማራጭ መምረጣቸውን አስረድተዋል። በቀጣይም የሀገርና ሕዝብን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት በማስጠበቅ ከክልሉና ፌደራል መንግስት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ከዚህ ውጭ ያለ አካሄድ የሽፍትነት ተግባር ነው፥ ዝና እና የግል ጥቅምን በማስቀደም የሚደረግ ጽንፍ የረገጠ የብሔርተኝነት ትግል የትም አያደርስም ብለዋል።   በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የጎጃም ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የፋይናንስ ኃላፊ ከፋለ አለሙ፥ ከዓመታት በፊት ጀምሮ ዘላቂ ሰላምን ለማውረድ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ንግግር መደረጉን አስታውሰዋል። በዚህም የተደረጉ ንግግሮች ፍሬ አፍርተው የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙም ሕዝብን፣ የድርጅቱን አመራርና የሠራዊት አባላት ያስደሰተ መሆኑን ገልጸዋል። ከቀድሞው ሕወሓት፣ ሻዕቢያ እና ግብጽ ጋር የሚደረግ የጥፋት ተልዕኮም ለአማራ ሕዝብም ሆነ ኢትዮጵያ የሚጠቅም ባለመሆኑ የሰላም አማራጭ መቀበላቸውን ተናግረዋል። መርህ የለሽ የትጥቅ ትግል ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው በማስቀረት ጫና እያሳደረ በመሆኑ ቀሪ በጫካ የሚገኙ የፋኖ አደረጃጀቶችም የሰላም አማራጭን እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል።   በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የወሎ ቤተ-አማራ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የሕዝብ አስተዳደርና ማኅበራዊ ጉዳይ ኃላፊ ግርማ እጅጋየሁ፥ በትጥቅ ትግል በነበሩባቸው ጥቂት ዓመታት የአማራን ሕዝብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉስቁልና እንዲያስተናግድ አድርጓል ብለዋል። በዚህም ትክክለኛውን የሰላም አማራጭ በመከተል የተሄደበት የተሳሳተ የውክልና ጦርነት በመተው የሰላም ስምምነት መምረጣቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም በቀድሞው ሕወሓት በሚያደርገው ድጋፍ አማራ እርስ በዕርሱ ዋጋ እየከፈለ መሆኑን በመገንዘብ ሌሎች በጫካ የሚገኙ አደረጃጀቶች የሰላም አማራጭ መቀበል እንደሚኖርባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። በመግለጫው ላይ ሌሎች የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት አመራሮች ተገኝተዋል።
በአማራ ክልል ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማረጋገጥ ወጣቱ የሚያደርገውን ተሳትፎ ማጠናከር ይጠበቅበታል
Dec 11, 2025 86
ደሴ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ወጣቱ በተደራጀ አግባብ የሚያደርገውን ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚጠበቅበት ተመላከተ። የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በደሴ ከተማ እየተወያዩ ነው። በመድረኩ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ እንዳመለከቱት፤ የክልሉን ሰላም በማፅናት የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን፣ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋት፣ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል፣ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን ለማልማት እየተሰራ ነው።   ይህም የማዕድን ሀብቶችን ጭምር ወደ ልማት በመቀየር የሕብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል። ለክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና መረጋገጥ የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተው ወጣቱ ጉልበቱን፣ እውቀቱን፣ አቅሙንና ጊዜውን ተጠቅሞ የተጀመሩ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ዳር እንዲደርሱ ተሳትፎውን በተደራጀ አግባብ በማጠናከር የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ለውይይትና ለንግግር አሁንም በሩ ክፍት መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህ ጎን ለጎን ሕግ የማስከበር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፣ ሕብረተሰቡን በማስተባበር በከተማው የሰፈነውን ሰላም በማስጠበቅ አስደናቂ የልማት ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል። በኮሪደር ልማት፣ በመንገድ፣ በሥራ እድል መፍጠሪያ ሸድ፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎችም አበረታች ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ለሕብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት በመስጠት የመልካም አስተዳደር ችግሮች እየተቃለሉ መምጣታቸውን አንስተዋል።   ለዚህም ወጣቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመው፤ ሰላሙን ዘላቂ በማድረግ ለማፅናት በሚደረገው ጥረትም ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጠልም አመልክተዋል። በመድረኩ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ወጣቶችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ፖለቲካ
በመደመር መንግስት እሳቤ የሀገርን የብልፅግና ጉዞ ለማሳካት እንሰራለን - አመራሮች
Dec 11, 2025 0
ሰቆጣ፣ ገንዳ ውሃ፣ ደብረ ብርሃን፣ ወልዲያ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በመደመር መንግስት እሳቤ የአካባቢን ፀጋ በማልማት የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ የአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢ አመራሮች ገለፁ። ‘’በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ’’ በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና የወሰዱ አመራሮች የማጠቃለያ ፕሮግራምና የልማት ስራዎች ጉብኝት ተካሄዷል። በዋግህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ሰቆጣ ከተማ ስልጠና ተሳታፊዎች መካከል አቶ አሻግሬ ደሳለኝ እና አቶ ታረቀ አለሙ እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት እሳቤ በህብረ ብሄራዊ መርህ ለሀገር ግንባታ መትጋት ነው።   የግብርናውን ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት የመላቀቅ ርዕይን ለማሳካት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ አክለዋል። ሌላዋ የስልጠናው ተሳታፊ ወይዘሮ ፀገነት ደምሴ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው ባገኙት እውቀት ህብረተሰቡ የተፋጠነ አገልግሎት እንዲያገኝ ሚናቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።   በተመሳሳይ በዞኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር የሀገሪቱን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥኑ ናቸው ያሉት ደግሞ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውኃና አካባቢው ያሉ የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሰልጣኞች ናቸው። የጉብኝቱ ተሳታፊ አቤሴሎም ጌታቸው እንዳሉት፤ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነውን አካባቢ ለአልሚዎች ይበልጥ ክፍት እንዲሆን የአመራርነት ሚናቸውን እንደሚወጡም አክለዋል።   ዮናስ ሞላልኝ እና አቶ አስማማው አለባቸው በበኩላቸው፤ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ሀብትን የማመቻቸት ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። መንግስት ያስቀመጣቸውን እድገት ተኮር ኢንሼቲቮች አሟጦ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ እንዳሉት፤ አመራሩ በጉብኝቱ የተመለከቷቸውን የልማት ተግባራት እንደየአካባቢያቸው ነባራዊ ሁኔታ ማስፋትና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢንዱስትሪ ዘርፉን በማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንን የገለፁት ደግሞ የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ደምሰው መንበሩ ናቸው። ባለፉት አምስት ወራት 32 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 211 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል። የጉብኝቱ ተሳታፊ አቶ ጥላየ ገብርየ እንዳሉት፤ ስልጠናውና በጉብኝቱ ሀገሪቱን ያለችበትን የእድገት ደረጃ ለመገንዘብ ያስቻለ ነው። ስልጠናው ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ኤልሳቤት ሀይለመስቀል ናቸው። የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ ከስልጠናው የተገኘውን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አገርን የመገንባትና የማዘመን ስራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከተማችንን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ሃብቶችን ማልማት ላይ ጠንክሮ ለመስራት የቤት ስራ የሰጠ ነው ብለዋል። በከተማ ግብርና፣ በወንዝ ዳርቻ ልማት፣ በሌማት ትሩፋትና በስራ እድል ፈጠራ የመደመር መንግስት ዕሳቤን የማሳኪያ ቁልፍ ስራዎች እንደሆኑም ገልጸዋል።
አመራሩ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል
Dec 11, 2025 13
ደሴ/ባሕርዳር፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፡-በተደመረ አቅምና እውቀት አመራሩ ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ሊያገለግል ይገባል ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ተናገሩ። "የመደመር መንግስት እይታ፣የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በደሴና ባሕርዳር ለመካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።   በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ፤ በየደረጃው ያለው አመራር ለልማት ከመትጋት ባለፈ በቀናኢነት ህዝብን ለማገልገል የላቀ ዝግጁነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት ጭምር የተሟላ ስብእና በመላበስ ለችግሮች መፍትሄ መሻት፣ለሰላምና ልማት በጋራ መትጋት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም አመራሩ በስልጠናው ያገኘውን ግንዛቤ በመሰነቅ በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል መዘጋጀት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የክልሉ መንግስት ከምንም በላይ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን፣ በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሃብትና ጸጋዎችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የማድረግ የተቀናጀ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል።   ከስልጠናው ታሳትፊዎች መካከል ወይዘሮ ሶፊና አደም እና አቶ ኡመር አሰፋ፤ ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት ተግባር ላይ በማዋል ውጤት ለማምጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በባሕርዳር ከተማ የማጠቃለያ መድረክ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን፤ ‎በግብርና፣በኢንዱስትሪ፣ በከተሞች መሰረተ ልማትና በቱሪዝም ብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት ዘርፎች ላይ የተሰጡ ስልጠናዎችን በተቀናጀ መልኩ በተግባር መግለጥ ይገባል ብለዋል።   የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሰፋ ጥላሁን፤ ‎የልማት እቅዶችን ማሳካት የሚቻለው በትብብር በመስራት በመሆኑ በዚሁ ልክ አመራሩ ዝግጁ ሆኖ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊ አመራሮችም በተደመረ አቅምና እውቀት ህዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።
በአማራ እና አፋር ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች የልማት ትስስሮችን ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Dec 11, 2025 13
ደሴ፤ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በአማራ እና አፋር ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች የሰላም ግንባታና የልማት ትስስሮችን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። የሁለቱ ክልሎች የሰላምና ፀጥታ አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በአዋሳኝ አካባቢዎች በዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች ዙሪያ በኮምቦልቻ ከተማ ውይይት አድርገዋል። የአማራ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር)፥የክልሎቹ አጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች ጠንካራ አብሮነት ያላቸው መሆኑንና የሚጋሯቸው በርካታ እሴቶች እንዳሏቸው አንስተዋል።   እነዚህን እሴቶች በማጎልበት የሰላም ግንባታና የልማት ትስስሮችን ይበልጥ ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አጽኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም በሁሉቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሰላም ግንባታን የማጎልበትና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል። በተለይም የመሰረተ ልማትና የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማጠናከር እንዲሁም ሰላምን በማጽናት ረገድ በቀጣይ የተቀናጀ ጥረት እናደርጋለን ሲሉ ተናግረዋል። የአፋር ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ኮሚሽነር አህመድ ሁመድ በበኩላቸው፥ በሁሉቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በሰላምና የልማት ስራዎች ጉዳይ ይበልጥ ተቀራርበን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።   በመሰረተ ልማትና የገበያ ትስስር እንዲሁም በሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ስለመሆኑም አንስተዋል። በመሆኑም እነዚህን አጠናክሮ በመቀጠል የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበልጥ ተቀናጅተን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። ግጭት ሰባቂዎችን በጋራ መመከትና የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ይገባል ያሉት ደግሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ቸሩጌታ ገነነ፤ በኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   ይሁን እንጂ በተለያዩ አካባቢዎች ከልማት ይልቅ ግጭትና አለመረጋጋት እንዲፈጠር የሚጥሩ የጥፋት ተልእኮ ያነገቡ አካላት ስለመኖራቸው አንስተው ሰላምን ማጽናትና ለልማት መትጋት የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል። በመሆኑም በአፋርና አማራ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አጽዕኖት ሰጥተዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምስራቅ እዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አሰፋ ቸኮል፤ በሁሉም አካባቢዎች ዘላቂ ሰላምን ማስጠበቅና የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት እውን ማድረግ የጋራ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል። በተለይም በአካባቢው በስፋት የሚስተዋለውን ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከል፣ የመሳሪያና ሌሎችም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን በጥብቅ መከታተልና በጋራ መከላከል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በመድረኩ የፌዴራል፣ የሁለቱ ክልልች እንዲሁም የዞንና የወረዳ አመራሮች፣ የፀጥታ አባላት እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች ነው
Dec 11, 2025 20
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ። በአፍሪካ ሕብረት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች ጉባዔ ተጠናቋል። ጉባኤው አህጉሪቱ እያጋጠሙ የሚገኙትን ሽብርተኝነት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና ሌሎች የደኅንነት ችግሮችን በተባበረ ክንድ መፍታት ላይ ያለመ ነው። መሪዎቹ የአፍሪካን የሠላምና የፀጥታ ችግሮች የሌላ አካል ጣልቃ ገብነት ሳይስፈልግ እንዴት በራስ አቅም ብቻ መፍታት እንደሚቻል በዝርዝር ተወያይተዋል።   ለቀናት በልዩ ልዩ አፍሪካዊ ጉዳዮች ሲመክር የቆዬው የመከላከያ መሪዎች ጉባኤ ቀጠናዊ ሠላምና መረጋጋትን ማስፈን፣ በሶማሊያ አልሸባብን ማስወገድ፣ በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ለሠላም ማስከበር ተልዕኮ የፋይናንስ ድጋፍ በሚሉትና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ የመፍትሔ አቅጣጫ አስቀምጧል። ኢትዮጵያ ለሠላም ባላት ጠንካራ አቋምና ተምሣሌትነት ተመርጣ ጉባኤውን ለተከታታይ ዓመታት እያስተናገደች መሆኗን ያነሱት የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት እየሠራች እንደምትገኝም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ የሚስተዋል ችግሮችን በፍጥነት የሚፈታ የተባበረ የአፍሪካ የተጠንቀቅ ኃይል አስፈላጊነት ላይ መወያየቱን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ለአህጉሪቱ ያላት አስተዋፅኦ የተንፀባረቀበት ጉባኤ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለሶማሊያ ሕዝብ ሠላም ላበረከተው አስተዋፅኦ በስብሰባው ከፍተኛ እውቅና መሰጠቱን ያወሱት በመከላከያ የዓለም አቀፍና የጎረቤት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ሰብስቤ ዱባ በቀጣይም የአህጉሪቱን ችግሮች በትብብር እየፈቱ ለመሄድ ከስምምነት መደረሱን ገልፀዋል።   ሁሉም የአፍሪካ አባል ሀገራት የሚሳተፉበት የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች የሠላምና ደኅንነት ጉባኤ በየዓመቱ የሚካሄድ መሁኑም ተመላክትል። 17ኛውን የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች ስብሰባ እና 20ኛው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሞችና የደህንነት ኃላፊዎች ስብሰባ ከህዳር 29 እስከ ታህሳስ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መካሄዱን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል።
የመደመር መንግስት እሳቤ ሀገር አሻጋሪ ራዕይ ያለው በመሆኑ ለተግባራዊነቱ እንተጋለን-አመራሮች 
Dec 11, 2025 86
ጎንደር ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፡- የመደመር መንግስት እሳቤ ሀገር አሻጋሪ ራዕይና ተልዕኮ ያለው በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ግንባር ቀደም በመሆን በቁርጠኝነት እንተጋለን ሲሉ የጎንደር ማዕከል ሰልጣኝ አመራሮች ተናገሩ። ከጎንደር ከተማ አስተዳደርና ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን የተውጣጡ አመራሮች በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል። ከሰልጣኝ አመራሮቹ ውስጥ አቶ ነጋ አሰፋ፤ የመደመር መንግስት እሳቤዎች ብዝሀ ኢኮኖሚን በመገንባት ለብልጽግና ጉዞ መሳካት ትልቅ የኢኮኖሚ ምሰሶ ነው ብለዋል።   መንግስት ለከተሞች ልማትና እድገት መፋጠን የጀመራቸው ተግባራት በከተሞች ድህነትና ስራ አጥነት ችግር በመፍታት በኩል ታላቅ ተስፋን የፈነጠቀ እርምጃ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ ሌላው ተሳታፊ አቶ ዋሲሁን ሞላ እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት እሳቤዎች በኢትዮጵያ ዘላቂና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገት እንዲመዘገብ የተቀመጠውን ግብ አመራሩ በቁርጠኝነት እንዲፈጽም ምቹ የፖለቲካ አውድ የሚፈጥር ነው፡፡ ስልጠናው የነበረብንን የአስተሳሰብና የእውቀት ክፍተቶች በመሙላት በቀጣይ ሀገር አሻጋሪ የሆነውን የመደመር መንግስት እሳቤዎች ከአካባቢያችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማዛመድ መተግበር እንድንችል አቅም ፈጥሮልናል ብለዋል፡፡ በቅርቡ የተፈረመው የዘላቂ ሰላም ስምምነት አዎንታዊ እርምጃ ከመሆኑም በላይ አመራሩና ሕዝቡ በቅንጅት እያከነወኑት ላለው የሰላም ግንባታ ተግባራት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡   የመደመር መንግስት እሳቤዎች ኢትዮጵያ ያሏትን እምቅ የልማት አቅሞችና የተፈጥሮ ሀብት ጸጋዎች እንድትጠቀም ምቹ ሀገር በቀል የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያመላከተ ነው ያሉት ደግሞ አቶ አበበ ጌጡ ናቸው፡፡ ስልጠናው የአመራሩን እሳቤዎችና እይታዎች በማሳደግ በተደመረ አቅም በመፍጠርና በመፍጠን መርህ የብልፅግና ጉዞው ስኬታማ እንዲሆን አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር እንደሆነ ጠቁመው ፤ ለተግባራዊነቱም ግንባር ቀደም በመሆን በቁርጠኝነት እንደሚተጉ ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ የተደረሰው የዘላቂ ሰላም ስምምነት መንግስት ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ጠቁመው፤ ሰላምን የማፅናቱ ተግባር እንዲሳካ በግንባር ቀደምትነት ጠንከረው እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡   በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች መልካም ተሞክሮ የሚቀሰምባቸው እንደሆኑ ሰልጣኝ አመራሮቹ ተናግረዋል፡፡ የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ስራም መንግስት ለታሪካዊ ቅርሶች ጥበቃ የሰጠው ትኩረት ማሳያ እንደሆነ አመልክተው፤ የከተማ ግብርና ስራዎችም የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ድርሻቸው የላቀ መሆኑን በምልከታው መገንዘባቸውን ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት፣ የከተማ ግብርና የቱሪዝም መዳረሻ ልማቶችንና ኢንዱስትሪዎችን እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በአካባቢው ያለውን አስተማማኝ ሰላም በማጽናት የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ በቅንጅት እየተሰራ ነው
Dec 11, 2025 83
ሐረር ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን አስተማማኝ ሰላም በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የምስራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ፍቃዱ ፀጋዬ ገለጹ። የምስራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች ክልሎች፣ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ ጥምር ግብረ ኃይል በሠላምና ፀጥታ ዙሪያ ውይይት አካሄደዋል።   የውይይቱ ዓላማም በዞኖች እና ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት የአካባቢውን ሠላም እና ፀጥታ የበለጠ አጠናክረው ለማስቀጠል ያለመ መሆኑ ታውቋል። የውይይት መድረኩን የመሩት የምስራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ፍቃዱ ፀጋዬ፤ በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን አስተማማኝ ሰላም በማዝለቅ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል። በተለይም አካባቢው ከፍተኛ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ የሚታይበትና አሸባሪዎች ሰላምን ለማናጋት የሚጥሩበት በመሆኑ የጸጥታ አካላት ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት ሌት ከቀን ለሰላም የሚሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።   የጸጥታ አካላት በቅንጅትና በትብብር የሰላም ዘብ ሆነው እየሰሩ መሆኑን አንስተው የሀገር መከላከያ ሰራዊትም ሰላምን በማጽናት የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የላቀ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የሐረሪ፣ በኦሮሚያ ክልል የምስራቅ እና የምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች፣ በሶማሌ ክልል የሲቲ እና የፋፈን ዞኖች፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና የማያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ አመራሮችና የፖሊስ ኮሚሽነሮች እንዲሁም የምስራቅ ዕዝ እና የፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በጫካ የሚንቀሳቀሱ አካላት የሀገርና ሕዝብን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ የሰላም አማራጭ ሊቀበሉ ይገባል - የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ከፍተኛ አመራሮች
Dec 11, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በጫካ የሚንቀሳቀሱ አካላት የሀገርና ሕዝብን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ የሰላም አማራጭ ሊቀበሉ እንደማገባ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ከፍተኛ አመራሮች አስታወቁ። የአማራ ሕዝብ በውክልና ጦርነት እንዲቆይ የሚሹ የጥፋት ተልዕኮዎችን በመተው ትክክለኛውን የሰላም ስምምነት አማራጭ መቀበላቸውንም ገልጸዋል። በአማራ ክልል መንግስትና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የተፈረመውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።   በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ምክትል የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊና የወሎ ቤተ-አማራ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ እያሡ አበራ፥ የአማራን ህዝብ ጥያቄ በትጥቅ ትግል እናስከብራለን በሚል በጫካ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በአማራ ክልል መንግስትና በሕዝባዊ ድርጅቱ የተፈረመው የሰላም ስምምነትም የአማራን ሕዝብ ክብርና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ባከበረ መንገድ የተፈጸመ መሆኑን ተናግረዋል። በተፈረመው የሰላም ስምምነትም በዘፈቀደ የተመራ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ዕውቅና ባለው መንገድ የተፈጸመ መሆኑንም አንስቷል። የአማራ ሕዝብ ከዚህ በላይ ጦርነትን የመሸከም አቅም የለውም፥ ሌሎች በጫካ የሚንቀሳቀሱ አካላትም የሕዝብና የሀገርን ጥቅምና ክብር በሚያስከብር አግባብ የሰላም አማራጭን መቀበል አለባቸው ብለዋል። በዚህም ለሕዝብ የሚበጅ ትክክለኛ የንግግር ውሳኔን በማሳለፍ የሰላም አማራጭ መምረጣቸውን አስረድተዋል። በቀጣይም የሀገርና ሕዝብን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት በማስጠበቅ ከክልሉና ፌደራል መንግስት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ከዚህ ውጭ ያለ አካሄድ የሽፍትነት ተግባር ነው፥ ዝና እና የግል ጥቅምን በማስቀደም የሚደረግ ጽንፍ የረገጠ የብሔርተኝነት ትግል የትም አያደርስም ብለዋል።   በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የጎጃም ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የፋይናንስ ኃላፊ ከፋለ አለሙ፥ ከዓመታት በፊት ጀምሮ ዘላቂ ሰላምን ለማውረድ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ንግግር መደረጉን አስታውሰዋል። በዚህም የተደረጉ ንግግሮች ፍሬ አፍርተው የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙም ሕዝብን፣ የድርጅቱን አመራርና የሠራዊት አባላት ያስደሰተ መሆኑን ገልጸዋል። ከቀድሞው ሕወሓት፣ ሻዕቢያ እና ግብጽ ጋር የሚደረግ የጥፋት ተልዕኮም ለአማራ ሕዝብም ሆነ ኢትዮጵያ የሚጠቅም ባለመሆኑ የሰላም አማራጭ መቀበላቸውን ተናግረዋል። መርህ የለሽ የትጥቅ ትግል ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው በማስቀረት ጫና እያሳደረ በመሆኑ ቀሪ በጫካ የሚገኙ የፋኖ አደረጃጀቶችም የሰላም አማራጭን እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል።   በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የወሎ ቤተ-አማራ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የሕዝብ አስተዳደርና ማኅበራዊ ጉዳይ ኃላፊ ግርማ እጅጋየሁ፥ በትጥቅ ትግል በነበሩባቸው ጥቂት ዓመታት የአማራን ሕዝብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉስቁልና እንዲያስተናግድ አድርጓል ብለዋል። በዚህም ትክክለኛውን የሰላም አማራጭ በመከተል የተሄደበት የተሳሳተ የውክልና ጦርነት በመተው የሰላም ስምምነት መምረጣቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም በቀድሞው ሕወሓት በሚያደርገው ድጋፍ አማራ እርስ በዕርሱ ዋጋ እየከፈለ መሆኑን በመገንዘብ ሌሎች በጫካ የሚገኙ አደረጃጀቶች የሰላም አማራጭ መቀበል እንደሚኖርባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። በመግለጫው ላይ ሌሎች የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት አመራሮች ተገኝተዋል።
በአማራ ክልል ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማረጋገጥ ወጣቱ የሚያደርገውን ተሳትፎ ማጠናከር ይጠበቅበታል
Dec 11, 2025 86
ደሴ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ወጣቱ በተደራጀ አግባብ የሚያደርገውን ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚጠበቅበት ተመላከተ። የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በደሴ ከተማ እየተወያዩ ነው። በመድረኩ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ እንዳመለከቱት፤ የክልሉን ሰላም በማፅናት የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን፣ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋት፣ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል፣ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን ለማልማት እየተሰራ ነው።   ይህም የማዕድን ሀብቶችን ጭምር ወደ ልማት በመቀየር የሕብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል። ለክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና መረጋገጥ የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተው ወጣቱ ጉልበቱን፣ እውቀቱን፣ አቅሙንና ጊዜውን ተጠቅሞ የተጀመሩ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ዳር እንዲደርሱ ተሳትፎውን በተደራጀ አግባብ በማጠናከር የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ለውይይትና ለንግግር አሁንም በሩ ክፍት መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህ ጎን ለጎን ሕግ የማስከበር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፣ ሕብረተሰቡን በማስተባበር በከተማው የሰፈነውን ሰላም በማስጠበቅ አስደናቂ የልማት ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል። በኮሪደር ልማት፣ በመንገድ፣ በሥራ እድል መፍጠሪያ ሸድ፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎችም አበረታች ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ለሕብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት በመስጠት የመልካም አስተዳደር ችግሮች እየተቃለሉ መምጣታቸውን አንስተዋል።   ለዚህም ወጣቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመው፤ ሰላሙን ዘላቂ በማድረግ ለማፅናት በሚደረገው ጥረትም ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጠልም አመልክተዋል። በመድረኩ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ወጣቶችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ማህበራዊ
የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ ነው
Dec 11, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማጠናከር የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የጤና ሚኒስቴር የእናቶች፣ የህፃናትና ወጣቶች ጤና አጠባበቅ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ አካሒዷል።   የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች። በተለይም የእናቶችና ህፃናት ጤና አጠባበቅ እና ተደራሽነት ላይ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል። እነዚህ ስኬቶች በመንግስት ቁርጠኝነት እና በአጋር አካላት ያልተቋረጠ ድጋፍ የተገኙ መሆናቸውን ገልፀዋል።   ኢትዮጵያ የእናቶችና ህፃናት ጤና በሁሉም የጤና ተቋማት በተሟላ መልኩ መስጠት የሚያስችል ጥረት እያደረገች ነው ያሉት ሚኒስትሯ፥ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማጠናከር የአጋር አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የእናቶችና የህጻናት ሞትን ለመቀነስ ያስቀመጠችውን ግብ ለማሳካት ዕቅድ ነድፋ እየሰራች መሆኑን አንስተዋል።   ለዚህ ሥራ ይበልጥ መጠናከር የሚውል የሀብት ማሰባሰብ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው እስካሁንም ከአጋር አካላት ከ160 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሃብት መሰብሰቡን ነው ያነሱት። ይህ ሃብት ከዚህ ዓመት ጀምሮ ለሦስት ዓመታት ጥቅም ላይ እንደሚውል በመጥቀስ የሀብት ማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የተሰበሰበው ሃብት ለህክምና ቁሳቁስና ግብዓት፣ ለጤና ተቋማት ግንባታ፣ ለጤና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታና መሰል ስራዎች እንደሚውል ሚኒስትር ዴኤታው አክለዋል።   በኢትዮጵያ የኔዘርላንድ አምባሳደርና የአጋር አካላት የሃብት ማሰባሰብ አስተባባሪ ክርስቲን ፒሬን፥ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያስመዘገበች ያለው ውጤት የሚበረታታ ነው ብለዋል። በተለይም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ሁሉም አጋር አካላት የሚከናወኑ ተግባራትን ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላቸው ጠቁመው መሰል የሃብት ማሰባሰብና የድጋፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ዩኒቨርሲቲው የክልሉን የሰው ሃብት እውቀትና ክህሎት ለማጎልበት በትኩረት እየሰራ ነው
Dec 11, 2025 43
ባህር ዳር፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦የክልሉን የሰው ሃብት እውቀትና ክህሎት ከማዳበር ባለፈ የመፈጸምና የማስፈጸም አቅምን የማሳደግ ተግባርን በትኩረት እያከናወነ መሆኑን የአማራ ክልል ስቴት ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። ስቴት ዩኒቨርሲቲው አዲስ የተቋቋመበትን አዋጅ እና ደንብ ለማስተዋወቅ ያለመ የውይይት መድረክ ዛሬ አካሄዷል። ‎የዩኒቨርሲቲው ‎ፕሬዝዳንት ማተብ ታፈረ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ዩኒቨርሲቲው በክልሉ ያለውን የሰው ሃብት የእውቀትና የክህሎት ክፍተት በመሙላት እንዲሁም የመፈጸምና የማስፈጸም አቅምን የማሳደግ ትልቅ ኃላፊነት አለበት።   ስቴት ዩኒቨርሲቲው የአጭር‎፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ስልጠናዎችን ከመስጠት በተጨማሪ ችግር ፈቺ የምርምርና የማማከር ስራዎችን እንደሚያከናውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው የምርምርና የማማከር ስራዎችን የውስጥ ገቢን በሚያሳድግ አግባብ እንደሚያከናውን ገልጸው በጥናት ላይ የተመሰረቱ አጫጭር ስልጠናና የረጅም ጊዜ ትምህርቶችን እየሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል። የክልሉ መንግስት በየጊዜው በሚያደርገው ግምገማ ትልቁ ክፍተት የሰው ሃብት ዕውቀትና ክህሎት እንዲሁም የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም ማነስ እንደሆነም የሚታወቅ ነው ብለዋል። ይህንን ችግር ለመቅረፍም ቀደም ሲል የአማራ ክልል የአመራር አካዳሚ ይባል የነበረውን ተቋም ወደ ስቴት ዩኒቨርሲቲነት በማሳደግ በተሻለ አቅም ስራዎችን እንዲያከናውን እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ስቴት ዩኒቨርሲቲው በእውቀትና በክህሎት የዳበረ የሰው ኃይል የማፍራት ሚናውን ለመወጣት እየሰራ መሆኑን የገለፁት ፕሬዝዳንቱ በየደረጃው ያለው የዩኒቨርስቲው ሰራተኛም ይህንኑ ታላቅ ኃላፊነት በመረዳት ተግቶ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በመድረኩም የስቴት ዩኒቨርስቲው አመራሮችና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በክልሉ የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Dec 11, 2025 44
ነቀምቴ ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እና ተሳትፎ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ''አካል ጉዳተኝነትን የሚያካትት ማህበረሰብ መገንባት ለተሻለ ማህበራዊ እድገት'' በሚል መሪ ሀሳብ የአካል ጉዳተኞች ቀን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በነቀምቴ ከተማ ተከብሯል።   መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ አብዱላሂ አህመድ፣ በክልሉ የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት እና ተሳትፎ ለማሳደግ በተሰራው ስራ ውጤት እየተገኘ መሆኑን ገልጸዋል። አካል ጉዳተኞችን ለማካተት፣ ለማሳተፍ እና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የወጡ ህጎች በአግባቡ እንዲተገበሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።   ከዚህ ጎን ለጎን በክልሉ የአካል ጉዳተኞች የተሀድሶ ማዕከል ማቋቋም፣ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታ መፍጠር እና ተያያዠ ስራዎች መሰራታቸውንም አስረድተዋል። በቀጣይም በክልሉ የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል አካል ጉዳተኞች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ደራራ ጣፋ እንደተናገሩት፤ ከለውጡ ወዲህ የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ነው።   ማህበረሰቡ አካል ጉዳተኝነትን በተመለከተ ያለው ግንዛቤ እንዲሻሻል ለማድረግም የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች በስፋት እየተሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ አካል ጉዳተኞችን በማህበር በማደራጀት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አመልክተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የነቀምቴ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ መላኩ ጌታሁን (ረዳት ፕሮፌሰር)፤ በከተማው ሁሉንም ማህበረሰብ ታሳቢ ያደረገ የልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።   በቀጣይም የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ በሚያሳድጉ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ የሚሰራበት ይሆናል ብለዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ኦላኒ አብዲሳ እንደተናገሩት፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለአካል ጉዳተኞች የሚሰጠው ትኩረት እየተሻሻለ መጥቷል።   መልካም ጅምሮች ቢኖሩም አሁንም አንድ አንድ የአገልግሎት መስጫ ቦታዎች ለአካል ጉዳተኞች የማይመቹ ሁኔታዎች በመኖራቸው መስተካከል አለበት ብለዋል። በክልሉ የአካል ጉዳተኛ ተሀድሶ ማዕከላትን ለማቋቋም እየተደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑንም አካል ጉዳተኞች ተናግረዋል።
ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ሚናችንን አጠናክረን እንቀጥላለን- የኃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች 
Dec 11, 2025 49
ገንዳ ውኃ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ሚናቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የዞኑ የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። በወቅታዊ የሰላም ግንባታና ሰላምን ማጽናት ላይ የኃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎችን ያሳተፈ የምክክር መድረክ ዛሬ በገንዳ ውኃ ከተማ ተካሄዷል።   ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የሀገር ሽማግሌው አቶ ሹመት ምስጋናው ፤ መንግስት ሕግ ከማስከበር ጎን ለጎን የሰላም በሮችን ክፍት አድርጎ ለሰላም ያሳየውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ሰላም የሁሉም መሰረት መሆኑን አንስተው፤ ወደ ሰላም የመጡ ወገኖች መንግስት የሰጣቸውን እድል ተጠቅመው የበደሉትን ሕዝብ እንዲክሱ ለማድረግ ሚናቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል። አሁን በአካባቢው የሰፈነው ሰላም እንዲመጣ ብዙ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው፤ በአካባቢው ሰላምን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወን ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። ሌላኛው ተሳታፊ ሸህ ሁሴን አህመድ በበኩላቸው፤ መንግስትና ሕዝብ እጅና ጓንት ሆነው በመስራት ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት የጀመሩትን ጥረት ማጠናከር እንዳለባቸው አመልክተዋል።   ለዚህም እንደ ሐይማኖት አባት ህብረተሰቡን በማስተማርና አጥፊዎችን በመገሰፅ ሰላምን ለማጠናከር እንሰራለን ያሉት የሃይማኖት አባቱ፣ ለዘላቂ ሰላም ሚናቸውን ይበልጥ እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል። ለዘላቂ ሰላም አጥብቀው እንደሚሰሩ የገለጹት ደግሞ አቶ ጓዴ አራጋው ናቸው። ችግሮች በሰላም እንዲፈቱ እንደሀይማኖት አባት የበኩላቸውን ጥረት ሲያደርጉ እንደቆዩ አስታውሰው፤ በቀጣይም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ሚናቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በበኩላቸው፤ በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ይበልጥ እንዲጠናከር ቅንጅታዊ ሥራው ይቀጥላል ብለዋል።   የሐይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ለሰላም ግንባታ የማይተካ ሚናቸውን በመወጣት እያበረከቱት ያለውን ሚና አጠናክረው እንዲቀጥሉም አመልክተዋል። በመከላከያ ሰሜን ምዕራብ ዕዝ የ504ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ቾምቤ ወርቁ፤ ሰላም በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ እንደማይመጣ ገልጸው፤ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ሥራ ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።   ማህበረሰቡ ከሠራዊቱ ጎን በመሰለፍ ለተገኘው ሰላም የጎላ ሚና መጫወቱን ጠቅሰው፤ ሰላሙን ለማፅናት በሚደረገው ጥረትም ሕብረተሰቡ ድጋፉን ማጠናከር እንዳለበት አመልክተዋል።
ኢኮኖሚ
በመዲናዋ የህዝብ እርካታን የሚያሳድጉ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 11, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የህዝብ እርካታን የሚያሳድጉ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥን የሚያሳልጡ ስማርት የወረዳ አስተዳደር ህንጻዎችን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።   ለምረቃ የበቁት የአስተዳደር ህንጻዎች በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ፣ በላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 እና ወረዳ 1 የሚገኙ ህንጻዎች ናቸው። ህንጻዎቹ የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በተናበበ እና በተሳለጠ መልኩ ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ ሲሆን የአገልግሎት መስጫ ቢሮዎች ፣የመሰብሰቢያ አዳራሾችና የመኪና ማቆሚያዎች የተሟሉላቸው ናቸው፡፡ ህንጻዎቹ የህጻናት ማቆያ፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን ጨምሮ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ የሆኑ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውም በዚሁ መርሐ ግብር ላይ ተመላክቷል፡፡   ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ እያደገ ለመጣው የህዝብ ፍላጎት ተመጣጣኝ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ዘመኑን የዋጁ አገልግሎቶች ተደራሽ ማድረግ ጊዜው የሚጠይቀው ነው፡፡   የከተማ አስተዳደሩ ቀልጣፋና የተናበበ አገልግሎት ለመስጠት የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል ። ዛሬ በሶስት ቦታዎች ላይ የተመረቁት ስማርት አገልግሎት መስጫ ህንጻዎች የዚህ ጥረት ማሳያ ናቸውም ብለዋል፡፡ አገልግሎት አሳጣጡ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን ከግንባታ ባሻገር ለሰው ሃይልም ሰፊ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡   አገልግሎት ሰጪዎች በክህሎት እና በአመለካከት የዳበሩ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ የመዲናዋ አመራሮች የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ዛሬ በይፋ የተመረቁት ስማርት አገልግሎት መስጫ ህንጻዎችን ደረጃ በደረጃ በሌሎች ክፍለ ከተሞችም የማስፋፋት ተግባራት እንደሚከናወን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የግልፅነት መርህ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደትን እያፋጠነ ነው
Dec 11, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የግልፅነት መርህ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችውን ሂደት እያፋጠነ መሆኑን የዓለም ንግድ ድርጅት አክሴሽን ዲቪዥን ዳይሬክተር ማይካ ኦሺካዋ ገለጹ፡፡ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር ሂደት እና በተከናወኑ ስራዎች ላይ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ለመፍጠር "ኢትዮጵያን በንግድ በማስተሳሰር፤ ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው ፎረም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል፡፡   የዓለም ንግድ ድርጅት አክሴሽን ዲቪዥን ዳይሬክተር ማይካ ኦሺካዋ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን የተቀመጡ መስፈርቶችን በፍጥነት እያካሄደች ትገኛለች ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የአባልነት ሂደት 22 ዓመታትን ማስቆጠሩን አስታውሰው አሁን ላይ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት አመርቂ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን ቀጣይነት ያለው ተሳትፎ እያከናወነች መሆኑን ጠቅሰው በቴክኒክ ደረጃ ሙሉ ለሙሉ የተጠናከረ የድርድር ሂደት እያካሄደች እንደምትገኝ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በስድስተኛው የድርድር ሂደት ለቀረቡላት ሁሉም ጥያቄዎች በቂ ምላሽ መስጠቷ የሀገር ውስጥ የፖሊሲ ጥንካሬዎችንና ውሳኔዎችን ያመላክታል ብለዋል፡፡ በድርድር ሂደቱ ሙሉ በሙሉ በሰነድ የተደገፈ ግብዓት ማቅረቧ ለገበያ ተደራሽነት ወሳኝ መሠረት ለመጣል እንደሚያስችላት ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዕቃዎችና አገልግሎቶች ዙሪያ ያቀረበችው የተመጣጠነ ዋጋ ጠንካራ እና ተዓማኒነት ያለው መሆኑን አስር አባል ሀገራት ማረጋገጣቸውን አስታውቀዋል፡፡ በዚህም አባል ሀገራቱ በፍጥነት ወደ ዝርዝር የቴክኒክ ድርድር ለመግባት ፍላጎት እንዳላቸው ማሳየታቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከ1 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት መቻሏን ጠቁመው ለዓለም የንግድ ድርጅት አባላት ያቀረበቻቸው የሕግ ሰነዶች 400 መድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡   ይህም በሌሎች ሀገራት የድርድር ሂደት ከታዩት እጅግ ከፍተኛው ቁጥር በመሆኑ ለዓለም ንግድ ድርጅት የግልጽነት መርህ ምሳሌ ሆናለች ብለዋል። ከድርድር ቡድኑ ሚና ባሻገርም የኢትዮጵያ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርም ለአባልነት ሂደቱ መፋጠን ወሳኝ አበርክቶ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ይህም የኢትዮጵያን የአባልነት ጉዞ ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ገልጸው ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ ጋር የሚጣጣም ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡
የገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት መርሃ ግብር ተጠቃሚዎችን የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ውጤት እያመጡ ነው 
Dec 11, 2025 69
ድሬዳዋ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦በድሬዳዋ አስተዳደር የገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት መርሃ ግብር ተጠቃሚዎችን የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር እና በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ኢብራሂም ዩሱፍ የውሃ መሳቢያ ሞተሮችን ለልማታዊ ሴፍትኔት ተጠቃሚ አርሶአደሮች አበርክተዋል።   ከንቲባ ከድር በወቅቱ እንዳሉት፤ የገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት መርሃ ግብር ተጠቃሚዎችን የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥና ከጥገኝነት ለማውጣት እየተሰሩ የሚገኙ ልማቶች ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ ናቸው። በአስተዳደሩ የተረጂነት አስተሳሰብ እየተለወጠ መሆኑን ጠቅሰው አርሶአደሩና አርብቶአደሩ ያለውን መሬት፣ ውሃ እና ጉልበት በማቀናጀት ውጤታማ ስራዎች እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።   መሬት ፆሙን እንዳያድር፣ ለውሃ ገብ የመስኖ ተጠቃሚዎች አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግና በዓመት ሶስት ጊዜ በማምረት ከቤተሰብ አልፎ ለገበያ ማቅረብ የጀመሩ ግንባር ቀደም አርሶአደሮች እየተፈጠሩ መሆኑን አንስተዋል። ዛሬ የተደረገው ድጋፍም የተጀመሩትን ሥራዎች ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እና ከጥገኝነት የወጣ ማህበረሰብ ለመገንባት አጋዥ እንደሚሆን አስታውቀዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው፤ ዛሬ የተደረገው ዘመናዊ የግብርና መሳሪያዎች ድጋፍ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመላቀቁን ጉዞ እንደሚያፋጥን ገልፀዋል።   ተረጂነትን ሙሉ በሙሉ የማጥፋቱ ጉዞ እንዲሳካ የሚደረገው የተቀናጀ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት በአስተዳደሩ አራቱም ክላስተሮች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በመሸጋገር ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የአነስተኛ መስኖና የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በብዛትና በጥራት መከናወናቸውን የገለፁት ደግሞ የድሬዳዋ ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ ናቸው።   አቶ ኑረዲን አክለውም፤ ዛሬ ለአርሶአደሮቹ በ8 ሚሊዮን ብር ተገዝተው ከተሰጡት የውሃ መሳቢያ ሞተሮች በተጨማሪ በልማታዊ ሴፍትኔት መርሃግብር የታቀፉ ከ7ሺህ 500 በላይ የቤተሰብ ሃላፊዎች በተለያዩ የገቢ አማራጭ ስራዎች ላይ እንዲሳተፉ የሚያስችሉ ስልጠናና የመነሻ ገንዘብ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል። በዚህ አመት መጨረሻ ከ26 ሺህ 970 በላይ የልማታዊ ሴፍትኔት ተጠቃሚዎች ራሳቸውን ችለው ከመርሃ ግብሩ እንደሚሰናበቱም አረጋግጠዋል። ዛሬ በተካሄደው ስነስርዓት ላይ ከውሃ መሳቢያ ሞተሮች በተጨማሪ በ6 ሚሊዮን ብር የተገዙ የመስክ ስራ የደህንነት መጠበቂያ ልብስና ቁሶች ለማህበረሰብ ስራ አስተባባሪዎች መበርከቱ ታውቋል።
በዞኖቹ ከ27 ሺህ 200 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ በበጋ መስኖ ስንዴ እየለማ ነው
Dec 11, 2025 62
ደብረ ማርቆስ/ ገንዳውሃ ፤ታህሳስ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ጎጃምና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች ከ27 ሺህ 200 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ በበጋ መስኖ ስንዴ እየለማ መሆኑን የየዞኖቹ ግብርና መምሪያዎች አስታወቁ። አርሶ አደሮች፤ ቀደም ሲል ጀምሮ በበጋ ስንዴ ልማት ላይ በመሳተፍ ውጤታማ መሆናቸውንና ልማቱን ዘንድሮም ለማጠናከር ግብአት እየተጠቀሙ ወደ ተግባር መግባታቸውን ተናግረዋል። የምሥራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ የመስኖ ልማት ቡድን መሪ አቶ ሃብታሙ ማህመድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዚህም እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ13 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ታርሶ በማለሰለስ ከዚህም 7 ሺህ 500 ሄክታር በዘር መሸፈኑን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም 12ሺህ ሄክታር መሬት በተመሳሳይ ለማልማት በሂደት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ለልማቱ በግብአትነት የሚውል ከ60 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ ቀርቦ ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን ተናግረዋል። 8 ሺህ 200 የውሃ መሳቢያ ሞተሮች ለአርሶ አደሮች መቅረቡን ጠቅሰው፤ ከሚለማው መሬትም ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል። በተመሳሳይ በምዕራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ የመስኖና ውሃ አጠቃቀም ባለሙያ አስናቀው አራጋው እንዳሉት፤ በዞኑ 2 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት እየተሰራ ነው። በልማቱ አርሶ አደሮች፣ ባለሃብቶችና ወጣቶች እየተሳተፉ ሲሆን፤ እስካሁን ከ400 ሄክታር በላይ መሬት ማልማት ተችሏል ብለዋል። ምርታማነትን ለማሳደግም ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት በማህበራት በኩል እየቀረበ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚለማው መሬትም 80 ሺህ ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል። በምሥራቅ ጎጃም ዞን ማቻከል ወረዳ የየውላ ቀበሌ አርሶ አደር አስከዚያ ምረት በሰጡት አስተያየት፤ ከግማሽ ሄክታር በላይ መሬት የበጋ ስንዴ ለማልማት በዝግጅት ላይ ነኝ ብለዋል። ባላፉት ሦስት ዓመታት በበጋ ስንዴ ልማት በመሳተፍ የተሻለ ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተው፤ ልማቱን ዘንድሮም ለማጠናከር የተሻለ ግብዓት በመጠቀም የበለጠ ተጠቃሚ ለመሆን ወደ ተግባር መግባታቸውን ተናግረዋል። የዚሁ ቀበሌ አርሶ አደር ጓዴነህ አንዷለም፤ ግማሽ ሄክታር መሬት በመስኖ ስንዴ ለማልማት እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፤ ባለፈው ዓመት አልምተው ለገበያ ካቀረቡት ምርት ተጠቃሚ እንደሆኑም አስታውሰዋል። በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ አርሶ አደር ይመር አበበ በሰጡት አስተያየት፤ በበጋ መስኖ ስንዴ ለመጀመሪያ ጊዜ ግማሽ ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል ማልማት እንደቻሉና የሰብሉ ቡቃያም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ሌላኛው ተሳታፊ ወጣት ይበልጣል አምሳሉ በበኩሉ እንዳለው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በመሳተፍ በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ተጨማሪ ገቢ የማግኘት እቅድ ይዞ እየሰራ ይገኛል። ከዚህ በፊት አካባቢው ለስንዴ ልማት አይሆንም የሚል እምነት ነበረን ያለው ወጣቱ ፤ ሆኖም ባለፉት ዓመታት አልምተው ተጠቃሚ የሆኑ ሰዎች በማየት ወደ ልማቱ መግባቱን ገልጿል። ከመደበኛ መስኖ በተጨማሪ በስንዴ ዘር የሸፈንኩት ግማሽ ሄክታር መሬት የቡቃያው ሁኔታ በጥሩ ደረጃ ላይ ነው ያሉት ደግሞ አርሶ አደር ሙሐመድ ስጦታው ናቸው። ካለሙት መሬትም የተሻለ ምርት በመሰብሰብ ተጠቃሚ ለመሆን በቂ ግብዓት መጠቀማቸውን ገልጸዋል።  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢንስቲትዩቱ የባዮቴክኖሎጂ ምርምሮችና ግኝቶችን ለማስተዋወቅ የተቀናጁ ተግባራትን እያከናወነ ነው
Dec 11, 2025 47
ሮቤ ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የባዮቴክኖሎጂ ምርምሮችና ግኝቶችን ለኅብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጁ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ገለጸ። የኢንስቲትዩቱ የግብርና ባዮ-ቴክኖሎጂ የደቡብ ምሥራቅ መድረክ (ኦፋብ ኢትዮጵያ) ከመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የባለድርሻ አካላት ዐውደ ጥናት በባሌ ሮቤ አካሂዷል።   በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የግብርና ባዮ -ቴክኖሎጂ የኢትዮጵያ አስተባባሪ ታደሰ ዳባ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ በባዮ ቴክኖሎጂ ሳይንስ የግብርናው ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው። ቴክኖሎጂው በግብርናው መስክ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።   ለአብነትም በባዮ ቴክኖሎጂ ሳይንስ በቆሎና የጥጥ ዝርያ ላይ እየተካሄዱ የሚገኙ ምርምሮች ተስፋ ሰጪ ውጤት ማምጣታቸውን አንስተዋል። የባዮቴክኖሎጂ ሳይንስ ጥቅምን በሕብረተሰቡ ዘንድ በአግባቡ እንዲታወቅና ተደራሽ እንዲሆን ተከታታይነት ያለው ግንዛቤ ለመፍጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር መሰራቱን አመልክተዋል። የባዮ ቴክኖሎጂ ሳይንስ በተለይ የግብርናው ምርታማነት ላይ ማነቆ የሆኑ የሰብል በሽታዎች፣ አረምና ሌሎች ችግሮችን ለማቃለል የሚያግዝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ ተስፋዬ ዲሳሳ (ዶ/ር) ናቸው።   በሀገሪቱ ባለፉት ዓመታት በቆሎን በማዳቀል ዘርፍ የተካሄዱ የምርምር ሥራዎች በሽታን የሚቋቋምና ምርታማነትን የሚያሻሽል ዘር መገኘቱን አንስተዋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ፣ ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራ በተጓዳኝ ችግር ፈቺ ምርምሮችን እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   ዩኒቨርሲቲው በተለይ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የተሻሻሉና የምርጥ ዝርያዎችንና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር ተደራሽ ማድረጉን ጠቅሰዋል። የተካሄደው መድረክም የተገኘውን ውጤት ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው አንስተዋል። የባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በተካሄደው የባዮቴክኖሎጂ ዘርፍ መድረክ ላይ የምርምር ውጤቶችና የዘርፉን እምቅ አቅም ለኅብረተሰቡ ለማስተዋወቅ የሚረዱ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
አውደ ጥናቱ ለኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ኃይል ልማት ቀጣይ ስራዎች መደላድል የሚሆን ግንዛቤ ተፈጥሮበታል
Dec 11, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦አውደ ጥናቱ ለኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ኃይል ልማት ቀጣይ ስራዎች መደላድል የሚሆን ግንዛቤ የተፈጠረበት መሆኑን የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ገለጸ። የመጀመሪያው ብሔራዊ የኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር ሚና እና ኃላፊነት የተቋም ትግበራ አውደ ጥናት ምክክር መድረክ ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሽፈራው ተሊላ በዚሁ ወቅት፥ የኒውክሊየር ኃይል ለኢነርጂ፣ ለግብርና፣ ለጤና እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገለጸዋል። የዚህ ኃይል አጠቃቀም በዓለም አቀፍ ሕግ የሚመራ መሆኑን ገልጸው ሀገራት ሊከተሏቸወ የሚገቡ ቅደም ተከተሎች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በአውደ ጥናቱ በሀገር ውስጥ ያሉ ባለድርሻ አካላት እና የሚመለከታቸው ሌሎች ተቋማት መሳተፋቸውንና ግንዛቤ መፈጠሩን ተናግረዋል። የኒውክሊየር ፕሮግራሙ ሀገራዊ ፕሮጀከት በመሆኑ ህብረተሰቡ ለስኬቱ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ ማስቻል ላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። በአውደ ጥናቱ በዓለም አቀፍ የሕግ ማእቀፎች እና ሊከናወኑ በሚገባቸው ስራዎች ላይ ውይይት መደረጉንም አመላክተዋል። የተቋማት አቅም እና የሰው ኃይል ግንባታ ሌላኛው በአውደ ጥናቱ በስፋት የተዳሰሰ መሆኑን ጠቁመዋል።   አውደጥናቱ በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ልማት ቀጣይ ስራዎች መደላድል የሚሆን ግንዛቤ የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል። በአውደ ጥናቱ ከተሳተፉት መካከል የውመን ኢን ኒውክሊየር ኢትዮጵያ ፕሬዝደንት አበባ ጌጡ፤ አውደ ጥናቱ በቂ ግንዛቤ ያገኙበት መሆኑን ገልጸዋል።   በተለይም የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ባስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ላይ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ነው የገለጹት። በቀጣይም በፕሮግራሙ ላይ የሴቶች አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንዲሆን በስልጠና እንዲሁም በተለያዩ አውደ ጥናቶች የማብቃት ስራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። በአውደ ጥናቱ ጥልቅ እውቀት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ በኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን የጨረራና ኒውክሊየር ቴክኖሎጂ የማሳወቅ እና ፈቃድ አሰጣጥ መሪ ስራ አስፈጻሚ ስሩር ከድር ናቸው። ተጨማሪ እውቀት በመፍጠር በዘርፉ የተሰማሩትን ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳ መሆኑን ተናግረዋል።
ፋይዳ መታወቂያ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው -ተቋማት
Dec 11, 2025 105
ሐረር፤ ታህሳስ 2/2018 (ኢዜአ) ፡- ፋይዳ ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በሐረሪ ክልል የሚገኙ የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ገለጹ። ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ ማድረግ አንዱ ነው። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ማንኛውም አገልግሎት ፈላጊ ዜጋ ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያን እንዲይዝ መንግስት የተለያዩ አማራጮችን መዘርጋቱ የዚሁ ጥረት አካል ነው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሐረሪ ክልል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። በሐረሪ ክልል ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽሕፈት ቤት ባለሙያ አቶ ዘኪ አብዱልማሊክ ፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተግባራዊ መደረጉ በተለይም ከዚህ በፊት በመታወቂያ ረገድ ይስተዋል የነበረው ማጭበርበር ችግር ማቃለሉን ገልጸዋል። ፋይዳ ከሲስተም ጋር የተሳሰረ በመሆኑ አንድ ሰው በአንድ ማንነትና በአንድ መታወቂያብቻ እንዲገለገል አድርጓል፣ የነበሩ ብልሹ አሠራሮችንም ሙሉ በሙሉ እንዳሰቀረ ተናግረዋል። የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ሁሉንም ዜጎች ተደራሽ ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ በሐረሪ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል ኢትዮ- ፖስታ በሚሰጠው አገልግሎት የካውንተር ባለሙያ አቶ አብዲሳ ተካ ናቸው። በተጨማሪም ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ለግለሰብም ሆነ ለሀገር ደሕንነት የጎላ ፋይዳ እንዳለውና እንደ ሀገር ለተጀመረው የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች አንዱ ማሳያ መሆኑንም አክለዋል። ሌላው በሐረሪ መሶብ የአንድ ማዕከል ኢትዮ-ፖስታ በሚሰጠው አገልግሎት የካውንተር ባለሙያ ዮሐንስ እስቂያስ በበኩላቸው፤ ፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ተቋማት ያለ ልዩነት አገልግሎት እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ሲል ተናግረዋል። በአገልግሎት ሰጪ እና ተቀባዩ መካከልም መተማመን እንዲፈጠር ያስቻለ ስለመሆኑም አንስተዋል። የሐረሪ ክልል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ኃላፊና የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ አስተባባሪ አቶ አርሰላን አብዲ ፤ በክልሉ እስካሁን 263ሺህ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ ተመዝግበው መውሰዳቸውንና ይህም ከእቅዱ በላይ ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በክልሉ የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ያልወሰዱ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል። የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እንደ ሀገር ለተጀመሩ የዲጂታላይዜሽን፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ስርዓት ግንባታ ፋይዳው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል። የሀገር እና ዜጎችን ደሕንነትን በማስጠበቅ ረገድ ጉልህ አአስተዋጽኦ አለው ያሉት ሃላፊው፤ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መያዝ እንደሚጠቅማቸው በመረዳት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።  
የኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ ለአፍሪካ ሀገራት ጭምር በምሳሌነት የሚወሰድ ነው
Dec 11, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ ለአፍሪካ ሀገራት ጭምር በምሳሌነት የሚወሰድ መሆኑን የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸኃፊ ዋምኬሌ ሜኔ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ሀገራትን የዕርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ ለማሳለጥ የጋራ መገበያያ ገንዘብን ሥራ ላይ ማዋል እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል። ሁለተኛው የኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ዓመታዊ ጉበዔ ተካሂዷል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ዋና ጸኃፊ ዋምኬሌ ሜኔ በጉባዔው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአፍሪካ በየዓመቱ የሚፈጸመውን የአምስት ቢሊዮን ዶላር የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ በማሳለጥም የአህጉሪቱን የጋራ መገበያያ ገንዘብ ግብ ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል። የአህጉሪቱ የንግድ ልውውጥ በሶስተኛ ወገን ገንዘብ ይፈጸማል ያሉት ዋና ጸኃፊው፤ ይህም አፍሪካውያን ለአላስፈላጊ ወጪ እንዲጋለጡ እያደረጋቸው መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራትን የዕርስ በዕርስ የንግድ ልውውጥ ወጪ ቆጣቢ፣ ዘመናዊና ፈጣን ለማድረግም አህጉራዊ የጋራ መጠቀሚያ ገንዘብን በሥራ ላይ ማዋል እንደሚገባ አስረድተዋል። በአህጉሪቱ የንግድ ልውውጥም ሀገራት በየራሳቸው ገንዘብ ግብይት የሚፈጽሙበትን ቀልጣፋ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም አብራርተዋል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናም የአፍሪካ ሀገራትን የንግድ ልውውጥ የሚያሳልጥ የአሰራር ሥርዓት ምክረ ሃሳቦችን በመፍጠር የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ዋና ጸሃፊው ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስኬታማ ስራ እየሰራች መሆኑንም ጠቁመዋል። በዲጂታል ክፍያ ስርዓት ፍትሐዊ የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ ለአፍሪካ ሀገራት ጭምር በምሳሌነት የሚወሰድ ሥራ እየሰራች መሆኗን ገልጸዋል።
ስፖርት
የባህል ስፖርት ውድድሮች የህብረተሰቡን እሴቶች ለማስተዋወቅ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራሉ
Dec 11, 2025 54
ጅማ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ የባህል ስፖርታዊ ውድድሮች የህብረተሰቡን እሴቶች በማስተዋወቅ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥሩ የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ገለጹ። የጅማ ዞን የወረዳዎች የባህል ስፖርት ውድድርና እና ኤግዚቢሽን መርሀ ግብር ዛሬ መካሄድ ጀመረ።   በመክፈቻ መርሀግብሩ ላይ የተገኙት የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር እንዳሉት፤ በዞን ደረጃ የሚካሄደው የባህል ስፖርት ውድድርና የባህል ኤግዚቢሽን ማህበረሰባዊ እሴቶችን ሳይበረዙ ለትውልዱ ለማስተላለፍ መደላድል ፈጥሯል። ስፖርታዊ ውድድሩ የህብረተሰቡን ባህላዊ እሴቶች በማስተዋወቅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን ለማጉላት እንደሚያግዝም ጠቁመዋል።   በዞኑ ያሉትን የባህል እሴቶች ለማህበረሰባዊ ትስስር ለማዋል መሰል ኤግዚቢሽኖች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን አክለዋል። የጅማ ዞን ስፖርት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ነጉማ መኮንን በበኩላቸው፤ የባህል ስፖርት ውድድር የስፖርቱን ዘርፍ ወንድማማችነትና እህትማማችነት የሚያጠናክር መሆኑን ጠቁመዋል።   ለ13 ቀናት በሚካሄደው የባህል ስፖርት ውድድሩ ከ20 ወረዳዎችና ከአንድ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የባህል ስፖርት ተወዳዳሪዎችና የባህል ቡድኖች እንደሚሳተፉ ተናግረዋል። በአስር የባህል የስፖርት አይነቶች ውድድር የሚደረግ መሆኑን ገልጸው የፈረስ ግልቢያ፣ የገበጣ፣ቀስት፣ ትግል እና የገና ጨዋታ ስፖርቶች ይገኙባቸዋል ብለዋል።
በተጠባቂው ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ሪያል ማድሪድን አሸነፈ
Dec 11, 2025 112
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሊግ ሻምፒዮንስ ሊግ ተጠባቂ መርሃ ግብ ማንችስተር ሲቲ ሪያል ማድሪድን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በሳንቲያጎ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኒኮ ኦራይሊ በጨዋታ እና አርሊንግ ሃላንድ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሮድሪጎ ለሪያል ማድሪድ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ላይ ማንችስተር ሲቲ በመጀመሪያው አጋማሽ እና ሪያል ማድሪድ በሁለተኛው አጋማሽ ብልጫ ወስደው ተጫውተዋል። ውጤቱን ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ በ13 ነጥብ ደረጃውን ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። የ15 ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ሪያል ማድሪድ በ12 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። አርሊንግ ሃላንድ በሻምፒዮንስ ሊግ በ50 ጨዋታዎች 51 ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል። በሌላኛው መርሃ ግብር አርሰናል ክለብ ብሩዥን 3 ለ 0 አሸንፏል። በጃን ብሬይዴል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኖኒ ማዱዌኬ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ጋብርኤል ማርቲኔሊ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። አርሰናል በ18 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። መድፈኞቹ በሻምፒዮንስ ሊግ ሁሉንም ጨዋታ ማሸነፍ ችለዋል። ክለብ ብሩዥ በአራት ነጥብ 31ኛ ደረጃን ይዟል። የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒኤስጂ ከአትሌቲኮ ቢልባኦ ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ጁቬንቱስ በጆናታን ዴቪድ እና ዌስተን ማኬኒ ግቦች ፓፎስን 2 ለ ዐ አሸንፏል። ቤኔፊካ ናፖሊን 2 ለ 0 አሸንፏል። ባየር ሌቨርኩሰን ከኒውካስትል ዩናይትድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ከቦዶ ግሊምት በተመሳሳይ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ዛሬ አስቀድመው በተደረጉ ጨዋታዎች አያክስ ካራባግን 4 ለ 2፣ ኮፐንሃገን ቪያሪያልን 3 ለ 2 አሸንፈዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ውጤታማ ናቸው
Dec 11, 2025 69
አዳማ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። የዘንድሮውን የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራን ስኬታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኙ የዘርፉ ሙያተኞችና የስራ ኃላፊዎችን ያሳተፈ የቅድመ ዝግጅት መድረክ በአዳማ ገልመ አባገዳ አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የቢሮው ኃላፊ ጌቱ ገመቹ በዚህ ወቅት እንደገለፁት ዘንድሮ የበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ዕቀባ ስራ በትኩረት ይከናወናል። በክልሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀው በዚህም የመሬት መራቆት፣ የአፈር መሸርሸር፣ የጎርፍና የድርቅ ስጋት መቀነሱን አስታውቀዋል። በተጨማሪም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራው የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ለመቋቋም፣ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ ዓምና የእርከን ማሰር፣ የአፈርና ውሃ ዕቀባ፣ የተፋሰስና በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራም የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ተግባር መከናወኑን አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ስራዎችም የከርሰ እና ገፀ ምድር የውሃ ሀብት እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመው የደረቁ ወንዞች፤ ጅረቶችና ሃይቆች መመለሳቸውን ተናግረዋል። በዚህም የበጋ መስኖ ስንዴን በበቂ የውሃ አቅርቦት ማልማት መቻሉን ገልጸው ለዓሣ ዕርባታና ለመጠጥ አገልግሎቶች እየዋሉ መሆኑንም ተናግረዋል። በተመሳሳይም ከሰውና እንስሳት ንኪኪ ነፃ ሆኖ ያገገመ መሬትን የደን ሀብቱን በመጠበቅ ለስራ ዕድል ፈጠራ ከማዋል ባለፈ ለንብ ማነብ ተግባር እየዋለ ይገኛል ብለዋል። በዘርፉ የተገኘውን ውጤት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ዘንድሮ የአፈርና ውሃ ዕቀባና የተፋሰስ ልማት ስራውን ለማከናወን ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። ለዚህም አምስት ሺህ 930 ተፋሰሶች መለየታቸውን ገልፀው በአፈርና ውሃ እቀባውና በተፋሰስ ልማት ስራው ዘጠኝ ነጥብ ስምንት ሚሊየን ህዝብን ለማሳተፍ በቂ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ-ግብር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በተግባር እያገዘ ይገኛል
Dec 11, 2025 104
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የከርሰ ምድር የውሃ አቅምን በማጎልበት የመስኖ እርሻዎች እንዲስፋፉ የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑም ተገልጿል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ተግባራዊ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክቷል፡፡ መርኃ-ግብሩ ለመጪው ትውልድ ተስፋ ብቻ ሳይሆን አሁን ያለውንም ትውልድ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ ሲሆን በስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አኳያ የራሱን ጉልህ ሚና እየተወጣ ነው፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ በብራዚል ቤለም በተካሄደው የዓለም የአየር ንብረት (COP-30) ጉባኤ ላይ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት (COP-32) ጉባኤን እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል። በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማትና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈጻሚ እና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የብሄራዊ ቴክኒክ ኮሚቴ ጸሃፊ ፋኑሴ መኮንን፤ የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እያደረገች ላለችው ጥረት ተግባራዊ ምላሽ እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን አርባ በመቶ የሚሆኑት ለምግብነት የሚውሉ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ አረንጓዴ አሻራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስና ለምነትን በመጨመር የግብርና ምርታማነት እንዲሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። የከርሰ ምድር የውሃ አቅምን በማሳደግ የመስኖ እርሻዎች እንዲስፋፉም የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት ለምግብነት አገልግሎት የሚውሉ አትክልትና ፍራፍሬዎችን ጨምሮ ሌሎች ችግኞች በስፋት የተተከሉ መሆናቸውን ጠቁመው፤ እነዚህም ለቤተሰብ የገቢ ምንጭና ለሥርዓተ ምግብ መሻሻልም ጉልህ ድርሻ ማበርከቱን ጠቅሰዋል፡፡ በአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር የተተከሉ ችግኞች ደን በመሆን ለማር ምርት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር የንብ አናቢዎችን ተጠቃሚነት እያሳደጉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በበርካታ ዘርፎች ሰፊ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር በተለይም የወጣቶችንና የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን እያሳደገ እንደሚገኝም አክለዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብር ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑና የተራቆቱ አካባቢዎች ወደ ምርታማነት እንዲለወጡ በማድረግ ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ የራሱን አስተዋጾኦ እያበረከተ መሆኑን አመላክተዋል፡፡      
በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ዕድልን ለማስፋፋት የግሉ ዘርፍ ሚና የጎላ ነው
Dec 10, 2025 118
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ዕድልን ለማስፋፋት የግሉ ዘርፍ ሚና የጎላ መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ”አረንጓዴ ስራዎች የተሻለ ነገ” በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ፎረምና ባዛር ማካሄድ ጀምሯል።   የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ መንግሥት በመደመር እሳቤ በኢኮኖሚ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልዱ ለማስረከብ በርካታ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል። ባለሃብቶችና ኢንተርፕራይዞች በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዙሪያ ያላቸውን ፈጠራና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያሳድጉ ፣ በተለይም በታዳሽ ሃይል ላይ የሚውል ካፒታል ፈሰስ ማድረግ፣ የኢኮኖሚ ኢኒሸቲቮችን ማገዝና ግብርናውን ማዘመን ላይ እንዲሳተፉ አሳስበዋል፡፡፡ ከነዚህ መካከል የሀገሪቱን የአየር ንብረት ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስራ ተጠቃሽ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግር በግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት፣ በአረንጓዴ ፈጠራ፣ ፋይናንስና ኢንተርፕርነርሺፕ ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ በአረንጓዴ የኢኮኖሚ ዘርፍ የሚፈጠር የስራ ዕድል ለኢትዮጵያ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ተግባሩ ከስራ፣ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ጋር ከተጣመረ ዘርፉን በፍጥነት ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚን በመጠቀም የስራ እድል ፈጠራን ለማስፋፋት የያዘቸውን ግብ እንድታሳካ አጋር አካላት የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።   በኢትዮጵያ የስዊድን ኤምባሲ ከፍተኛ የፕሮግራም ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኒኮላ ኤሪክሰን አረንጓዴ የስራ ዕድል ፈጠራ ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችውን ሽግግር ለማገዝና የማይበገርና የተሰባጠረ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ ታዳሽ የሃይል አቅርቦትና ትራንስፖርት፣የአየር ብክለት ልቀት ቅነሳ፣የቆሻሻ አወጋገድ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ በማደግ ላይ የሚገኙ አማራጮች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ይህንን እውን ማድረግ የሚችል በእውቀት የበለጸገና ጠንካራ ወጣት ሃይል አላት ብለዋል፡፡    
በምዕራብ ጎንደር ዞን የበጋ ወቅት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ተጀመረ
Dec 10, 2025 105
ገንዳውሃ፤ ታህሳስ 1/2018(ኦዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን በተለያዩ ተፋሰሶች የበጋ ወቅት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ መጀመሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ ዛሬ በተጀመረው በዚሁ ሥራ ላይ የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የፌዴራል ፖሊስና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉ ሲሆን፤ ሥራው ለ30 ቀናት እንደሚቆይ ተነግሯል ፡፡ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በዞኑ በአራት ወረዳዎችና ሶስት ከተማ አስተዳደሮች በሚተገበረው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ 2ሺ 300 ሄክታር የተጎዳ መሬት ይለማል። ከዚህ ውስጥ በዛሬው ማስጀመሪያ ፕሮግራም በተለያዩ ቀበሌዎች 110 ተፋሰሶች ላይ መከናወኑን አንስተዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ተግባር በወል መሬቶችና በግል ይዞታዎች የሚሰራ ሲሆን፤በዚህም የውሃ እቀባ፣ እርከን ሥራና ሌሎች ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል። በዘመቻ በሚካሄደው በዚህ የልማት ሥራ ከ36 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን ለማሳተፍ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አስረድተዋል። አርሶ አደሮቹ የተፋሰስ ልማት ሥራዎቹን ቀጣይነት ያለው ቁጥጥርና ክትትል በማድረግ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸውን ለማጉላት በተለየው መሬት ላይ ዕፅዋቶች እንዲያለሙ እንደሚደረግ ገልጸዋል። በሰሜን ምዕራብ ዕዝ የ504ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቾምቤ ወርቁ በበኩላቸው፤ ሰራዊቱ ሰላምና ዳር ድንበርን ከማስከበር በተጨማሪ በልማት ሥራዎች በመሳተፍ ለሀገር እድገት የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። በበጋ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በተከናወነበት ሥፍራ ክረምት ላይ ችግኝ በመትከል የሚሳተፉ መሆኑንም ጠቁመዋል። በዞኑ የገንዳውኃ ዙሪያ አርሶ አደር አየነው ያሲን በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ዓመታት በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ላይ ተሳትፈው መልካም ውጤት በማየታቸው በዚህ ዓመት ሥራውን አጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በወል መሬት ላይ በተከናወነው እርከንና ችግኝ ተከላ ልማት አፈሩ ተሸርሽሮ ከጥቅም ውጭ የነበረ ስፍራ አገግሞ ለከብት መኖና የከርሰ ምድር ውሃን በማጎልበት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸውም አውስተዋል።   በበጋ የአፈርና ውሃ የጥበቃ ሥራዎች የለሙ ተፋሰሶች ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው የገለጹት ሌላኛው አርሶ አደር የሱፍ ዳምጤ ናቸው።  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 430
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል።   በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው።   አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 406
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 755
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 644
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ሐተታዎች
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 72
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል።   ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ።   ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡   የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።  
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 609
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 797
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 826
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 259
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2873
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2814
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3713
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2161
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1400
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7215
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5708
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58009
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52728
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33407
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30932
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26762
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25514
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25085
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25062
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58009
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52728
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33407
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30932
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 598
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው።   እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም።   የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል።   የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል።   ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!
ብልህ ከችግር ይማራል!!
Dec 2, 2025 391
ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል!! በማሙሽ ጋረደው ገራድ ተስፋዬ ተፈራ ትውልድና እድገታቸው በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ቃልሻ ቀበሌ ሲሆን በ1999 ዓ.ም በህገ ወጥ መንገድ ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው እንደነበር ያስታውሳሉ። ገንዘብ ለማግኘትና የመለውጥ ህልማቸውን ለማሳካት በሚል ሩቅ አስበው የጀመሩት ህገ ወጥ ጉዞ መዳረሻውን እስር ቤት አደረገው። ይህም ሁኔታ ''ሩቅ አሳቢ-ቅርብ አዳሪ'' አደረጋቸው። በባዕድ አገር በነበራቸው የ2 ዓመት የእስር ቤት ቆይታም የምግብ እጦትን ጨምሮ አካላዊ ጥቃትና ጉልበት ብዝበዛ እንዲሁም የተለያዩ ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶችን እንዳስተናገዱ ይናገራሉ።   ይህም አልበቃ ብሎ ከአካባቢው በህገወጥ መንገድ የሚሰደዱ ወጣቶችን ጉልበት በመጠቀም ሰፋፊ እርሻዎች ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ የጉልበት ብዝበዛ ይፈፀምባቸው እንደነበርም ያስታውሳሉ። ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል! የሚሉት ገራድ ተስፋዬ ሩቅ ሳይጓዙ፣ ገንዘብ ሳያወጡ ሰርተው መለወጥ የሚችሉበትን አካባቢያቸውን ፀጋ ሳያማትሩ ስደት መሄዳቸው ቁጭት ፈጥሮባቸው ነበር፡፡ ይህም በሀገራቸው እንኳንስ የለማን መሬት ይቅርና የተቦረቦረ መሬትን አልምቶ ጉልበትንና ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል ከእስር ቤት ቆይታቸው ተምረው ከእስር እንደተፈቱም ወዲያውኑ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል። በ2001 ዓ.ም ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሱም በማህበር ተደራጅተው ከመንግሥት ባገኙት 70 ሺህ ብር ብድር በእንስሳት እርባታ ላይ ለመሰማራት 4 የወተት ከብቶችን ገዝተው የእርባታ ስራ መጀመራቸውን ይገልጻሉ፡፡   በዚህም የዞኑ አስተዳደር የሰጣቸውን መሬት አልምተው የእንስሳት እርባታውን አስፋፍተው መስራት ጀመሩ፡፡ አሁን ላይ የወተት ላሞቹን ቁጥር 37 በማድረስ የወተት ምርታማነታቸው አድጎ ከቤት ፍጆታ አልፎ ለሆሳዕና ከተማና አካባቢው በቀን ከ670 ሊትር በላይ ወተት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ለ40 ወጣቶችም ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ከመፍጠራቸውም ባሻገር የተለያዩ የጭነትና የስራ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራት መቻላቸውን ይናገራሉ። የጀመሩትን ስራ በጥምር ግብርና የማስፋትና የሚያገኙትን ወተት በማቀነባበር ምርቱን በተለያየ መልኩ ለገበያ የማቅረብ ራዕይን ሰንቀው በትጋት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በህገወጥ ስደት ካጋጠማቸው ችግር ተነስተው በተግባር ያዩትን ለሌሎች በማስተማር የስደትን አስከፊነት ለአካባቢያቸው ወጣቶች እያስገነዘቡ መሆኑን ገልጸዋል።   ወጣቶች የስደትን አማራጭ ከመመልከታቸው በፊት የአካባቢያቸውን ፀጋ እንዲቃኙና ራዕይ ሰንቀው ራሳቸውን ለማሻሻል እንዲሰሩም መክረዋል። መለወጥ በውጪ ሀገር ብቻ ያለ የሚመስላቸው የቤተሰብ ኃላፊዎችም ልጆቻቸው በሀገራቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ በማመን ሊያግዟቸው እንደሚገባም አቶ ገራድ አስገንዝበዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደስላሴ፤ በክልሉ በርካታ ወጣቶች ያልተጨበጠ ተስፋ ሰንቀው ለህገወጥ ስደትና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡   በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ የሚያስችል አቅም በግብርናው ዘርፍ መኖሩን ጠቅሰው በዘርፉ የተሰማሩ ከስደት ተመላሾች በአካባቢያቸው ሰርተው ለስኬት እየበቁ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ላይ የሚገኙና የእነዚህን አካላት ተሞክሮ በመውሰድ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም