ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማለፍ አልቻለም
May 23, 2026 296
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ ከ17 ዓመት በታች ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ በተደረገ የመለያ ጨዋታ ሞዛምቢክ ኢትዮጵያን በመለያ ምት አሸንፋለች። በመሐመድ ስድስተኛ ስፖርት ኮምፕሌክስ በተካሄደው ጨዋታ አሚር ሚስባህ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ጎል ኢትዮጵያን መሪ አድርጓል። ዲዬጎ ፔሌምቤ በ57ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ባሳረፋት ጎል ሞዛምቢክ አቻ ሆናለች። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት በመጠናቀቁ ወደ መለያ ምት አምርቷል። በመለያ ምቱም ሞዛምቢክ 5 ለ 4 በማሸነፍ በኳታር አስተናጋጅነት ለሚከናወነው 21ኛው ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ ማለፏን አረጋግጣለች። እንየው ስለሺ ከኢትዮጵያ በኩል ፍጹም ቅጣት ምቱን የሳተ ተጫዋች ነው። በአሜሪካዊው አሰልጣኝ ቤንጃሚን ዚመር የሚመራው ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማለፍ አልቻለም። በሌላኛው የመለያ መርሐ ግብር ጋና ከዩጋንዳ ምሽት አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አዘጋጇ ሞሮኮ፣ ግብጽ፣ ኮትዲቯር፣ ካሜሮን፣ ታንዛንያ፣ ማሊ፣ ሴኔጋል እና አልጄሪያ በቀጥታ ወደ ዓለም ዋንጫ ያለፉ ሀገራት ናቸው። 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ እስከ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። በአፍሪካ ዋንጫው እየተሳተፉ ካሉ 16 ሀገራት መካከል 10ሩ በጥቅምት እና ህዳር ወር 2019 ዓ.ም በኳታር ለሚካሄደው 20ኛው የፊፋ ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ተሳታፊ ይሆናሉ። በዓለም ዋንጫው ላይ 48 ሀገራት ይሳተፋሉ።
በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት የሚደረገው ጥረት ውጤት እያመጣ ነው
May 23, 2026 239
ድሬደዋ፣ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት የሚያደርገው ጥረት ውጤት እያመጣ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። የባለ 6 ወለል ህንፃ ግንባታን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እና የኮርፖሬሽኑ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ኃይለብርሃን ዜና አስጀምረዋል። በወቅቱም የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንደገለፁት፤ ኮርፖሬሽኑ በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት የሚያደርገው ጥረት ውጤት እያመጣ ነው። ኮርፖሬሽኑ በድሬደዋ የመኖሪያ እና የንግድ ሞሎችን ተደራሽ ለማድረግ የጀመራቸው ስራዎች አበረታች በመሆናቸው ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል። የኮርፖሬሽኑ የኮርፖሬት ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኃይለብርሃን ዜና በበኩላቸው፤ ኮርፖሬሽኑ የመኖሪያ ቤት ችግርን ከመሰረቱ ለመፍታት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ውጤት እንደተመዘገበባቸው መሆኑን አመልክተዋል። ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ እየተመዘገቡ የሚገኙ የዘርፉ ለውጦችን በድሬዳዋ ለመድገም ጥናትን መሠረት ባደረገ መልኩ 13 ህንፃዎችን ለመገንባት ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በዛሬው ዕለት የተከናወነው የህንፃ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰው የኮርፖሬሽኑ 50ኛ ዓመት ምስረታ የማጠቃለያ በዓል በቀጣዩ ሰኞ በድሬዳዋ እንደሚከበርም አስታውቀዋል። ኮርፖሬሽኑ በቤቶች ልማት ዘርፍ እመርታዊ ለውጥ በማምጣት ችግሮችን በላቀ ደረጃ እየፈታ መሆኑን የገለፁት ደግሞ በኮርፖሬሽኑ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እውነቱ ወርቅነህ ናቸው። ኮርፖሬሽኑ የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት በአዲስ አበባ በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበሩን ገልፀው የዚሁ ክብረ በዓል ቀጣይ ክፍል በድሬዳዋ ከግንቦት 10/2018 ዓ/ም ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል ብለዋል። በ8 ሺህ 500 ካሬም ሜትር ስፋት ላይ የሚገነባው ዘመናዊ ህንፃ ለንግድ፣ ለመዝናኛ እና ለቢሮ አገልግሎቶች የሚውሉ የተለያዩ ክፍሎችን ያካተተ መሆኑም በስነ-ስርዓቱ ላይ ተመላክቷል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር እና ሌሎች የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና የኮርፖሬሽኑ ምክትል ስራ አስፈፃሚዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 250
ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
ሁል ሲቲ ከዘጠኝ ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ተመለሰ
May 23, 2026 232
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ሻምፒዮምሺፕ የጥሎ ማለፍ የፍጻሜ ጨዋታ ሁል ሲቲ ሚድልስቦሮውን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በዌምብሌይ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኦሊ ማክበርኒ በ94ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በጨዋታው ሚድልስቦሮው ብልጫ ቢውስድም ሁል ሲቲ በባከነ ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፈው ግብ አሸናፊ አድርጎታል። ውጤቱን ተከትሎ ሁል ሲቲ ከዘጠኝ ዓመታት በኋላ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መመለሱን አረጋግጧል። ክለቡ ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ ላይ የተወዳደረው እ.አ.አ 2016/17 ነበር። ሚድልስቦሮው ከዘጠኝ ዓመታት በኋላ ወደ ሊጉ የመመለስ ህልሙ ሳይሳካ ቀርቷል። ኮቨንተሪ ሲቲ እና ኢፕስዊች ታውን አስቀድመው ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ማደጋቸውን ያረጋገጡ ክለቦች ናቸው።
ሰው ተኮሩ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ዘርፈ-ብዙ እፎይታ እየሰጠ ነው
May 23, 2026 248
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ ሰው ተኮሩ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ዘርፈ-ብዙ እፎይታ እየሰጠ መሆኑን ተጠቃሚዎች ገለጹ፡፡ በአዲስ አበባ የተገነቡት የምገባ ማዕከላት መንግስት ለሰው ተኮር ልማት የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ያሳያሉ። ማዕከላቱ በቀን አንድ ጊዜ መመገብ የማይችሉ በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን፣ የከፋ የጤና ችግር ያለባቸውንና ጧሪ የሌላቸውን አረጋውያን በቋሚነት በየዕለቱ በመመገብ ላይ ይገኛሉ። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ቁጥር 20 የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል በቀን 500 ለሚሆኑ አቅመ ደካሞችና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ዜጎች ምገባ ያከናውናል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡት የማዕከሉ ተጠቃሚ እርቄ መኩሪያው፤ በተቋሙ አማካኝነት የዕለት ጉርሳቸውን ያለመቸገር እያገኙ መሆኑን ገልጸው፣ መንግሥት ለዜጎቹ የሚያደርገውን የሰብዓዊ ድጋፍና እንክብካቤ በእጅጉ አድንቀዋል። በአሁኑ ወቅት የምገባ ማዕከሉ በተለይም በከፍተኛ የኑሮ ውድነትና ጫና ውስጥ ለሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ትልቅ እፎይታን የሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላኛው ተጠቃሚ እናኒ ካሰይ በበኩላቸው፤ ከማዕከሉ የተመጣጠነ ምግብ እያገኙ መሆኑን ጠቅሰው፤ የከተማ አስተዳደሩ ይህንን መሰል በጎ ተግባር በማከናወኑ ሊመሰገን ይገባዋል ብለዋል። በምገባ ማዕከሉ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው መሰረት ጉታ እና የሺ ብርሃኔ የራሳቸውን ኑሮ ዘላቂ በሆነ የገቢ ምንጭ መደገፍ መጀመራቸውን ተናግረዋል። አስተያየት ሰጪዎቹ ማዕከሉ ከፈጠረላቸው የተሻለ የገቢ ዕድል ባሻገር፣ በየዕለቱ አቅመ ደካማ ወገኖቻቸውን በቅርበት ማገልገላቸው ትልቅ ሰብዓዊና የመንፈስ እርካታ እንዳጎናጸፈላቸውም ገልጸዋል። በርካታ የሥራ ፈላጊ ማኅበረሰብ ክፍሎች አዲስ ተስፋና የተረጋጋ የሕይወት መሠረት እየጣለ እንደሚገኝም አስረድተዋል። በመሆኑም መሰል ሰው ተኮር ማዕከላት መስፋፋታቸው በየአካባቢው ያለውን የሥራ አጥነት ጫና ለመቀነስና ማኅበራዊ ትስስርን ለማጠናከር ያለው ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ምሥክርነታቸውን ሰጥተዋል። የአዲስ አበባ የምገባ ኤጀንሲ ምክትል ዳይሬክተር ስንታየሁ ማሞ እንዳሉት፤ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላት ለአቅመ ደካሞች፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለወላጅ አልባ ሕፃናትና ለሀገር ባለውለታ ዜጎች አለኝታነታቸውን በተግባር እያሳዩ ነው። በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ በሚገኙ 29 የምገባ ማዕከላት ለተጠቃሚዎች ንጹህና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ እየተደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል። ይህ ሰው ተኮር ሥራ ስኬታማ ሊሆን የቻለው መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ባለሀብቶች እንዲሁም በጎ ፈቃደኛ ዜጎች ለፕሮግራሙ እያበረከቱ ባለው ቀና ድጋፍ መሆኑን አስገንዝበዋል። መርሐ-ግብሩ ወገኖችን ከመደገፍ ባለፈ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህልን እንዲሁም ማኅበራዊ መስተጋብርን በእጅጉ ያጠናከረ መሆኑንም ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ጠቅላላ ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት ሊሳተፉ ይገባል
May 23, 2026 389
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት እናታለም እንዳለ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር "በፖለቲካ፣ በምርጫና ሰላም ግንባታ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ማጎልበት" በሚል መሪ ሃሳብ ከማህበሩ አባላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። የማህበሩ ፕሬዚዳንት እናታለም እንዳለ በዚሁ ወቅት፤ ማህበሩ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና እኩል ተሳታፊነትን የማረጋገጥ ዓላማ ይዞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሴቶች የመምረጥና የመመረጥ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በመንግስት አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ የነቃ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚያግዙ የአቅም ግንባታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 2 ሺህ 200 የማህበሩ አባል የሆኑ ሴቶች ሰልጥነው የታዛቢነት ፍቃድ መውሰዳቸውንም ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሌሎችም ዕድሜያቸው ለምርጫ የደረሱ የማህበረሰብ ክፍሎች በምርጫው በመሳተፍ የሚመራቸውን መንግስት በድምፃቸው መምረጥ እንዲችሉ የማስገንዘብ ስራ እያከናውኑ መሆኑን ገልጸዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም ሴቶች በሃገር ሰላምና ፖለቲካ ውስጥ ያላቸውን የላቀ ፋይዳ በመገንዘብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድርሻቸውን እንዲወጡ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል። ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል። የህብረተሰቡ ግንዛቤ ለማሳደግ ቤት ለቤት በመሄድና የተለያዩ መርሃግብሮችን በማዘጋጀት ለምርጫው አሳታፊነት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የገለጹት የማህበሩ አባል ወይዘሮ መሰረት ሶርሳ ናቸው። ወይዘሮ አዳነች አሉላ በበኩላቸው፤ ለምርጫ የደረሱ ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ በማስተማር የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ከ513 ሺህ በላይ አባላት እንዳለው ተመላክቷል።
በዞኑ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ
May 23, 2026 265
ሰቆጣ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ የልማት ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ ብልፅግና ፓርቲን የሚደግፍ የአደባባይ ሰልፍ ተካሄዷል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው (ዶ/ር)፣ የለውጡ መንግስት የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፋፊ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በብሔረሰብ አስተዳደሩም የህዝቡን ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የልማት ስራዎችን በተሻለ ፍጥነትና ጥራት ለማስቀጠል፣ ህብረተሰቡ የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ በኩል እያበረከተ ያለውን ሚና አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የዞኑ ነዋሪም ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንታይቱ ካሴ በበኩላቸው፤ በዞኑ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል መርህ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረት በብሔረሰብ አስተዳደሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ህብረተሰቡ ለአካባቢው ሰላም አበክሮ መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በድጋፍ ሰልፉ የተሳተፉት ወይዘሮ ካሰች ውቡ ለአካባቢያቸው ሰላም መረጋገጥ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ ጌታቸው መንግስቴ፣ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በወሰድነው የምርጫ ካርድ መንግስት ሆኖ ይመራናል፣ ያስተዳድረናል ብለን የምናምነውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 23, 2026 292
ባህር ዳር፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ በወሰድነው የምርጫ ካርድ መንግስት ሆኖ ይመራናል፣ ያስተዳድረናል ብለን የምናምነውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። አስተያየታቸውን ከሰጡ ነዋሪዎች መካከል ገብረስላሴ ሳህሌ እንደገለጹት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገርን የሚመራ መንግስት ለመመስረት የህዝቡ ድምጽ የማይተካ ሚና አለው። ስለ ምርጫው ሂደትና አስፈላጊነት በቂ ግንዛቤ እየጨበጥኩ በመሆኑ በወሰድኩት የምርጫ ካርድ መንግስት ሆኖ ይመራኛል፣ ያስተዳድረኛል ብዬ ያመንኩበትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብለዋል። ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ ትዕግስት አበጀ በበኩላቸው፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይወክለኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ምርጫ ማለት የሀገርን እጣ ፈንታ በራስ ድምጽ መወሰን መሆኑን ጠቁመው፤ ፓርቲዎች በሚዲያ በሚያደርጉት ቅስቀሳ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ሊያረጋግጥ ይችላል የሚሉትን እየለዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ የበኩሉን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ የገለጸው ደግሞ ወጣት ደጀኔ አለምነው ነው። በወሰድኩት የምርጫ ካርድ ለወጣቱ ልዩ ትኩረት የሚሰጠውን፣ ለሀገር ልማትና ዕድገት ይበጃል ያልኩትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ሲል ገልጿል።
በለውጡ ዓመታት የመንግስት አገልግሎት ተደራሽነትን ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል
May 23, 2026 387
አገና፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በለውጡ ዓመታት የህዝብ ተጠቃሚነት እና የመንግስት አገልግሎት ተደራሽነትን ያረጋገጡ የአሰራር ስርዓቶች በመዘርጋታቸው ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ (ዶ/ር) ገለጹ። በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ አገና ከተማ፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን የሚደግፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በወቅቱ ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ሳይፈቱ የቆዩ የልማትና የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ የተደረጉ ጥረቶች ተጨባጭ ውጤት አስመዝግበዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሰረታዊ ማሻሻያ በመጣቱ በጤና፣ በትምህርት እንዲሁም በከተማና ገጠር ልማት ሁለተናዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ ውጤቶች ታይተዋል ብለዋል። በተለይም በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን በተቀናጀና በዘላቂነት ለመፍታት የተከናወኑ ተግባራትን ጠቅሰዋል። ለአብነትም የ"መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተለያዩ ከተሞች ወደ ስራ የገባው ይህ አሰራር፣ በርካታ ተቋማትን በአንድ ስፍራ በማቀፍ የተገልጋዩን ጊዜና ጉልበት የቆጠበ ከመሆኑም በላይ ቀደም ሲል ያጋጥም የነበረውን እንግልት በከፍተኛ ደረጃ አስቀርቷል ብለዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፣ መንግስት የህዳሴ ግድብን ባሳካው ልክ የባህር በር ለማግኘት የሚያስችሉ የዲፕሎማቲክ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንን ታላቅ እቅድ በላቀ ተነሳሽነት ለማሳካት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ርብርብ እንዲያደርግ አሳስበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይግለጡ አብዛ በበኩላቸው፤ በለውጡ ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። የመደመር መንግስት ለውጤት እንዲበቃ በማድረግ በኩል ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን በወቅቱ ጀምሮ በማጠናቀቅ ረገድ ተምሳሌት መሆን ችሏል ነው ያሉት። በክልሉ በገጠርና በከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ስኬታማ በመሆኑ የህዝቡን የአኗኗር ዘይቤ በመቀየር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ማጎልበት እንደተቻለም አስረድተዋል። የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘውዱ ዱላ በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸውና የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ለውጤት መብቃታቸውን ገልጸዋል። ይህም አገሪቱ ከተረጂነት ለመውጣት ለምታደርገው ጥረት ጠንካራ መሰረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመዋል። የሰልፉ ተሳታፊ የነበሩት አቶ መክብብ ገብረፃዲቅ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በውጤታማነት የመለሱ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ህብረተሰቡ በአንድነትና በመተባበር መለወጥ እንደሚቻል ያሳየ በመሆኑ ልማቱ እንዲቀጥል የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ብልፅግና ፓርቲ ዜጎችን ከድህነት በማውጣት የሀገርን እድገትና ማንሰራራት እውን የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል - ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)
May 23, 2026 362
ጅማ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ ዜጎችን ከድህነት በማውጣት የሀገርን እድገትና ማንሰራራት እውን ለማድረግ የጀመራቸውን ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በሚወዳደሩበት ኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሸቤ ሶምቦ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳ አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ በለውጡ ዓመታት ብልፅግና ፓርቲ የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ለማድረግና ሀገርን ከድህነት ለማውጣት ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም በመስኖ ስንዴ ልማት አስደናቂ ውጤት መገኘቱን አንስተው በሌሎችም መስኮች ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል። በመሆኑም ብልፅግና ፓርቲ ዜጎችን ከድህነት በማውጣት የሀገርን እድገትና ማንሰራራት እውን ለማድረግ የጀመራቸውን ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል። የሸቤ ሶምቦ ወረዳ አስተዳዳሪ መሀመድሳኒ አባኦሊ፤ ብልፅግና ፓርቲ በለውጡ ዓመታት ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን በማከናወን የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ማድረግ ችሏል ብለዋል። በተለይም በግብርና ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት ለመውጣት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። የሸቤ ሶምቦ ወረዳ በሩዝ ምርት የሚታወቅ መሆኑን አስታውሰው፤ ባለፉት ጥቂት አመታት ምርቱ በእጥፍ እንዲያድግ የተደረገበትን ስኬት ለአብነት አንስተዋል።
በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ተጠቃሚነታችንን ይበልጥ የሚያሳድግ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 23, 2026 339
ወልቂጤ ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ተጠቃሚነታችንን ይበልጥ የሚያሳድግ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በጉራጌ ዞን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ አካል ጉዳተኞች ተናገሩ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳ። በዘንድሮው የመራጮች ምዝገባ ከ50 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የመራጭነት ካርድ ወስደው ቀኑን እየተጠባበቁ ሲሆን፣ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ፖሊሲና ፕሮግራሞቻቸውን በምርጫ ቅስቀሳና በሚዲያ አማራጮች እያስተዋወቁ ነው። ኢዜአ በጉራጌ ዞን ያነጋገራቸው አካል ጉዳተኞች እንደገለጹት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለአካል ጉዳተኞች የተሰጠውን ትኩረትና ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድግ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል። በዞኑ የአካል ጉዳተኞች ማህበራት ህብረት ፕሬዝዳንት አቶ ዓብይ ጀማል በሰጡት አስተያየት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለአካል ጉዳተኞች ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ ከምዝገባ ሒደት ጀምሮ በተለያዩ ተግባራት ላይ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት የምርጫ ዓመታት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጓቸው ክርክሮች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የሚሰጡት ትኩረት አናሳ ነበር፤ በዚህ ዙር ግን ምርጫውን አካታች ለማድረግ የሚደረጉ አበረታች ጥረቶችን ታዝበናል ብለዋል። በዞኑ በምርጫው ቅድመ ዝግጅት ወቅት የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ የተሻለ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ዓብይ፤ ከ23 ሺህ በላይ አካል ጉዳተኞች ካርድ መውሰዳቸውንና 54 ታዛቢዎች ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በአግባቡ በመጠቀም ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን አረጋግጠዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ ወጣት ነፃነት ፍቅሬ በበኩሉ፤ የምርጫ ጣቢያዎች አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ አድርገው መደራጀታቸው ተሳትፏቸውን በእጅጉ እንዳሳደገው ገልጿል። የተፈጠረውን ምቹ መደላድል በመጠቀም በምርጫው ዕለት ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አክሏል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኃን በሚያደርጉት የ"ይምረጡኝ" ክርክር ቅስቀሳ እና የማኒፌስቶ ማስተዋወቅ ላይ አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረጉ ዕቅዶች ሲንጸባረቁ መመልከታቸው እንዳስደሰታቸው የገለጹት ደግሞ አቶ ፈቀደ ባደታ ናቸው። ምርጫው የሀገር ሰላምና የዜጎችን ደህንነት የሚያረጋግጥ እንዲሆን እንደሚመኙ ጠቅሰው፤ ለአካል ጉዳተኞች መብትና ተጠቃሚነት የሚቆረቆር ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮው የምርጫ ሂደት ለአካል ጉዳተኞች የተሰጠው ትኩረት እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣት ፈይሰል ሙደርም፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ዝጁ መሆኑን አረጋግጧል።
ለምርጫው በስኬት መጠናቀቅ የበኩላችንን እየተወጣን ነው - ተፎካካሪ ፓርቲዎች
May 23, 2026 365
ባህር ዳር፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ በስኬት መጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ እንደሚገኙ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ ተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በምርጫው ለመወዳደር የተመዘገቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምርጫው ለሀገር አንድነትና ለሕግ የበላይነት መረጋገጥ ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ እስካሁን ተሳትፏቸውን እያጠናከሩ መጥተዋል። መራጩ ሕዝብ በድምፁ የሚፈልገውን ፓርቲ ወደ ሥልጣን ለማምጣት የወሰደውን የምርጫ ካርድ በአግባቡ ይዞ፣ በምርጫው ዕለት በአግባቡ እንዲጠቀምበትም ፓርቲዎቹ መልእክት አስተላልፈዋል። የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴሃን) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ገብረመስቀል አደመ እንደገለጹት፤ ፓርቲያቸው የምርጫው ሂደት ፍትሃዊና አሳታፊ እንዲሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል። ፓርቲያቸው እስካሁን ለአባላቱና ለደጋፊዎቹ የምርጫ ሕጉንና የፓርቲውን ማኒፌስቶ መሠረት በማድረግ ግንዛቤ መፍጠሩን አውስተዋል። የሰለጠነ የፖለቲካ ትግል መገለጫው የሚፈልጉትን ፓርቲ በካርድ ወደ ሥልጣን ማምጣት መሆኑን መራጩ ሕዝብ መገንዘብ እንዳለበትም ገልጸዋል። በዚህም መራጩ ሕዝብ ያወጣውን የምርጫ ካርድ በአግባቡ በመያዝ፣ በዕለቱ ሀገርና ሕዝብን ያሻግራል ብሎ ያመነበትን ፓርቲ እንዲመርጥ መልእክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የሰሜን ኢትዮጵያ አስተባባሪና የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ሃይለማሪያም ብርሃኑ በበኩላቸው፤ በሕዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው መንግሥት ለመመስረት ምርጫ ዋናው መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል።
ካርዳችንን በጥንቃቄ በመያዝ የምንፈልገውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል -የገንዳ ውሃ ከተማና የጋዚግብላ ወረዳ ነዋሪዎች
May 23, 2026 333
ሰቆጣና ገንዳውኃ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጠቅላላ ምርጫው ለመሳተፍ የወሰድነውን ካርድ በጥንቃቄ በመያዝ ለሁሉም የሚጠቅም ፖሊሲ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በአማራ ክልል የገንዳ ውሃ ከተማና የጋዚግብላ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ። ነዋሪዎቹ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በወሰድነው ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ተጠቅመን ለህዝብና ለሀገር ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። በጠቅላላ ምርጫው ለመሳተፍ የወሰድነውን ካርድ በጥንቃቄ በመያዝ ለሁሉም የሚጠቅም ፖሊሲ ያለውን ፓርቲ እንመርጥበታለን ብለዋል። ከገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ዮሴፍ አየነው የመምረጥ መብቴን ተጠቅሜ የዜግነት ግዴታዬን ለመወጣት ተዘጋጅቻለሁ ሲሉ ተናግረዋል። ያወጣሁትን ካርድም ለህዝብ ተጠያቂ የሚሆንና ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ይገነባል ብዬ ለማምነው ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት እውን መሆን የድርሻዬን እወጣለሁ ብለዋል። ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ቤዛ አለሙ በበኩላቸው ሰላምና ዴሞክራሲን ለሚያሰፍን ፓርቲ ድምጻቸውን እንደሚሰጡ ተናግረዋል። "ካርዴን በወቅቱ ወስጃለሁ፤ በምርጫው ቀን በጠዋት ተገኝቼ ድምፄን በመስጠት ኃላፊነቴን እወጣለሁ" ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በዋግ ኽምራ ዞን የጋዝጊብላ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር ምስጋናው መኮነን ያወጡትን ካርድ አርሶ አደሩን የሚጠቅም ፖሊሲ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ እንደሚጠቀሙበት ተናግረዋል። "የምንፈልገውን ፓርቲ ለመምረጥ ሰላም ወሳኝ ነው" ያሉት አርሶ አደሩ የአካባቢያቸውን ሰላም በንቃት በመጠበቅና የመኸር እርሻ ዝግጅታቸውንም እያከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል። "የፖለቲካ ፓርቲዎች እያደረጉት ያለው ቅስቀሳ የሚበጀንን ፓርቲ ለመለየት አግዞናል" ያሉት ደግሞ ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ሞገስ ደባሽ ናቸው። ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የአካባቢያቸውን ሰላም አፅንተው እየጠበቁ መሆኑን ጠቁመው በድምፅ መስጫው ቀን ማልደው በመነሳት ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ፖለቲካ
ጠቅላላ ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት ሊሳተፉ ይገባል
May 23, 2026 389
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት እናታለም እንዳለ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር "በፖለቲካ፣ በምርጫና ሰላም ግንባታ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ማጎልበት" በሚል መሪ ሃሳብ ከማህበሩ አባላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። የማህበሩ ፕሬዚዳንት እናታለም እንዳለ በዚሁ ወቅት፤ ማህበሩ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና እኩል ተሳታፊነትን የማረጋገጥ ዓላማ ይዞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሴቶች የመምረጥና የመመረጥ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በመንግስት አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ የነቃ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚያግዙ የአቅም ግንባታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 2 ሺህ 200 የማህበሩ አባል የሆኑ ሴቶች ሰልጥነው የታዛቢነት ፍቃድ መውሰዳቸውንም ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሌሎችም ዕድሜያቸው ለምርጫ የደረሱ የማህበረሰብ ክፍሎች በምርጫው በመሳተፍ የሚመራቸውን መንግስት በድምፃቸው መምረጥ እንዲችሉ የማስገንዘብ ስራ እያከናውኑ መሆኑን ገልጸዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም ሴቶች በሃገር ሰላምና ፖለቲካ ውስጥ ያላቸውን የላቀ ፋይዳ በመገንዘብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድርሻቸውን እንዲወጡ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል። ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል። የህብረተሰቡ ግንዛቤ ለማሳደግ ቤት ለቤት በመሄድና የተለያዩ መርሃግብሮችን በማዘጋጀት ለምርጫው አሳታፊነት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የገለጹት የማህበሩ አባል ወይዘሮ መሰረት ሶርሳ ናቸው። ወይዘሮ አዳነች አሉላ በበኩላቸው፤ ለምርጫ የደረሱ ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ በማስተማር የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ከ513 ሺህ በላይ አባላት እንዳለው ተመላክቷል።
በዞኑ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ
May 23, 2026 265
ሰቆጣ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ የልማት ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ ብልፅግና ፓርቲን የሚደግፍ የአደባባይ ሰልፍ ተካሄዷል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው (ዶ/ር)፣ የለውጡ መንግስት የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፋፊ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በብሔረሰብ አስተዳደሩም የህዝቡን ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የልማት ስራዎችን በተሻለ ፍጥነትና ጥራት ለማስቀጠል፣ ህብረተሰቡ የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ በኩል እያበረከተ ያለውን ሚና አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የዞኑ ነዋሪም ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንታይቱ ካሴ በበኩላቸው፤ በዞኑ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል መርህ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረት በብሔረሰብ አስተዳደሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ህብረተሰቡ ለአካባቢው ሰላም አበክሮ መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በድጋፍ ሰልፉ የተሳተፉት ወይዘሮ ካሰች ውቡ ለአካባቢያቸው ሰላም መረጋገጥ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ ጌታቸው መንግስቴ፣ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በወሰድነው የምርጫ ካርድ መንግስት ሆኖ ይመራናል፣ ያስተዳድረናል ብለን የምናምነውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 23, 2026 292
ባህር ዳር፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ በወሰድነው የምርጫ ካርድ መንግስት ሆኖ ይመራናል፣ ያስተዳድረናል ብለን የምናምነውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። አስተያየታቸውን ከሰጡ ነዋሪዎች መካከል ገብረስላሴ ሳህሌ እንደገለጹት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገርን የሚመራ መንግስት ለመመስረት የህዝቡ ድምጽ የማይተካ ሚና አለው። ስለ ምርጫው ሂደትና አስፈላጊነት በቂ ግንዛቤ እየጨበጥኩ በመሆኑ በወሰድኩት የምርጫ ካርድ መንግስት ሆኖ ይመራኛል፣ ያስተዳድረኛል ብዬ ያመንኩበትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብለዋል። ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ ትዕግስት አበጀ በበኩላቸው፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይወክለኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ምርጫ ማለት የሀገርን እጣ ፈንታ በራስ ድምጽ መወሰን መሆኑን ጠቁመው፤ ፓርቲዎች በሚዲያ በሚያደርጉት ቅስቀሳ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ሊያረጋግጥ ይችላል የሚሉትን እየለዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ የበኩሉን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ የገለጸው ደግሞ ወጣት ደጀኔ አለምነው ነው። በወሰድኩት የምርጫ ካርድ ለወጣቱ ልዩ ትኩረት የሚሰጠውን፣ ለሀገር ልማትና ዕድገት ይበጃል ያልኩትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ሲል ገልጿል።
በለውጡ ዓመታት የመንግስት አገልግሎት ተደራሽነትን ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል
May 23, 2026 387
አገና፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በለውጡ ዓመታት የህዝብ ተጠቃሚነት እና የመንግስት አገልግሎት ተደራሽነትን ያረጋገጡ የአሰራር ስርዓቶች በመዘርጋታቸው ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ (ዶ/ር) ገለጹ። በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ አገና ከተማ፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን የሚደግፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በወቅቱ ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ሳይፈቱ የቆዩ የልማትና የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ የተደረጉ ጥረቶች ተጨባጭ ውጤት አስመዝግበዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሰረታዊ ማሻሻያ በመጣቱ በጤና፣ በትምህርት እንዲሁም በከተማና ገጠር ልማት ሁለተናዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ ውጤቶች ታይተዋል ብለዋል። በተለይም በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን በተቀናጀና በዘላቂነት ለመፍታት የተከናወኑ ተግባራትን ጠቅሰዋል። ለአብነትም የ"መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተለያዩ ከተሞች ወደ ስራ የገባው ይህ አሰራር፣ በርካታ ተቋማትን በአንድ ስፍራ በማቀፍ የተገልጋዩን ጊዜና ጉልበት የቆጠበ ከመሆኑም በላይ ቀደም ሲል ያጋጥም የነበረውን እንግልት በከፍተኛ ደረጃ አስቀርቷል ብለዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፣ መንግስት የህዳሴ ግድብን ባሳካው ልክ የባህር በር ለማግኘት የሚያስችሉ የዲፕሎማቲክ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንን ታላቅ እቅድ በላቀ ተነሳሽነት ለማሳካት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ርብርብ እንዲያደርግ አሳስበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይግለጡ አብዛ በበኩላቸው፤ በለውጡ ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። የመደመር መንግስት ለውጤት እንዲበቃ በማድረግ በኩል ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን በወቅቱ ጀምሮ በማጠናቀቅ ረገድ ተምሳሌት መሆን ችሏል ነው ያሉት። በክልሉ በገጠርና በከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ስኬታማ በመሆኑ የህዝቡን የአኗኗር ዘይቤ በመቀየር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ማጎልበት እንደተቻለም አስረድተዋል። የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘውዱ ዱላ በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸውና የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ለውጤት መብቃታቸውን ገልጸዋል። ይህም አገሪቱ ከተረጂነት ለመውጣት ለምታደርገው ጥረት ጠንካራ መሰረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመዋል። የሰልፉ ተሳታፊ የነበሩት አቶ መክብብ ገብረፃዲቅ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በውጤታማነት የመለሱ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ህብረተሰቡ በአንድነትና በመተባበር መለወጥ እንደሚቻል ያሳየ በመሆኑ ልማቱ እንዲቀጥል የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ብልፅግና ፓርቲ ዜጎችን ከድህነት በማውጣት የሀገርን እድገትና ማንሰራራት እውን የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል - ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)
May 23, 2026 362
ጅማ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ ዜጎችን ከድህነት በማውጣት የሀገርን እድገትና ማንሰራራት እውን ለማድረግ የጀመራቸውን ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በሚወዳደሩበት ኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሸቤ ሶምቦ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳ አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ በለውጡ ዓመታት ብልፅግና ፓርቲ የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ለማድረግና ሀገርን ከድህነት ለማውጣት ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም በመስኖ ስንዴ ልማት አስደናቂ ውጤት መገኘቱን አንስተው በሌሎችም መስኮች ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል። በመሆኑም ብልፅግና ፓርቲ ዜጎችን ከድህነት በማውጣት የሀገርን እድገትና ማንሰራራት እውን ለማድረግ የጀመራቸውን ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል። የሸቤ ሶምቦ ወረዳ አስተዳዳሪ መሀመድሳኒ አባኦሊ፤ ብልፅግና ፓርቲ በለውጡ ዓመታት ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን በማከናወን የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ማድረግ ችሏል ብለዋል። በተለይም በግብርና ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት ለመውጣት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። የሸቤ ሶምቦ ወረዳ በሩዝ ምርት የሚታወቅ መሆኑን አስታውሰው፤ ባለፉት ጥቂት አመታት ምርቱ በእጥፍ እንዲያድግ የተደረገበትን ስኬት ለአብነት አንስተዋል።
በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ተጠቃሚነታችንን ይበልጥ የሚያሳድግ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 23, 2026 339
ወልቂጤ ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ተጠቃሚነታችንን ይበልጥ የሚያሳድግ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በጉራጌ ዞን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ አካል ጉዳተኞች ተናገሩ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳ። በዘንድሮው የመራጮች ምዝገባ ከ50 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የመራጭነት ካርድ ወስደው ቀኑን እየተጠባበቁ ሲሆን፣ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ፖሊሲና ፕሮግራሞቻቸውን በምርጫ ቅስቀሳና በሚዲያ አማራጮች እያስተዋወቁ ነው። ኢዜአ በጉራጌ ዞን ያነጋገራቸው አካል ጉዳተኞች እንደገለጹት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለአካል ጉዳተኞች የተሰጠውን ትኩረትና ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድግ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል። በዞኑ የአካል ጉዳተኞች ማህበራት ህብረት ፕሬዝዳንት አቶ ዓብይ ጀማል በሰጡት አስተያየት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለአካል ጉዳተኞች ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ ከምዝገባ ሒደት ጀምሮ በተለያዩ ተግባራት ላይ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት የምርጫ ዓመታት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጓቸው ክርክሮች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የሚሰጡት ትኩረት አናሳ ነበር፤ በዚህ ዙር ግን ምርጫውን አካታች ለማድረግ የሚደረጉ አበረታች ጥረቶችን ታዝበናል ብለዋል። በዞኑ በምርጫው ቅድመ ዝግጅት ወቅት የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ የተሻለ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ዓብይ፤ ከ23 ሺህ በላይ አካል ጉዳተኞች ካርድ መውሰዳቸውንና 54 ታዛቢዎች ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በአግባቡ በመጠቀም ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን አረጋግጠዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ ወጣት ነፃነት ፍቅሬ በበኩሉ፤ የምርጫ ጣቢያዎች አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ አድርገው መደራጀታቸው ተሳትፏቸውን በእጅጉ እንዳሳደገው ገልጿል። የተፈጠረውን ምቹ መደላድል በመጠቀም በምርጫው ዕለት ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አክሏል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኃን በሚያደርጉት የ"ይምረጡኝ" ክርክር ቅስቀሳ እና የማኒፌስቶ ማስተዋወቅ ላይ አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረጉ ዕቅዶች ሲንጸባረቁ መመልከታቸው እንዳስደሰታቸው የገለጹት ደግሞ አቶ ፈቀደ ባደታ ናቸው። ምርጫው የሀገር ሰላምና የዜጎችን ደህንነት የሚያረጋግጥ እንዲሆን እንደሚመኙ ጠቅሰው፤ ለአካል ጉዳተኞች መብትና ተጠቃሚነት የሚቆረቆር ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮው የምርጫ ሂደት ለአካል ጉዳተኞች የተሰጠው ትኩረት እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣት ፈይሰል ሙደርም፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ዝጁ መሆኑን አረጋግጧል።
ለምርጫው በስኬት መጠናቀቅ የበኩላችንን እየተወጣን ነው - ተፎካካሪ ፓርቲዎች
May 23, 2026 365
ባህር ዳር፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ በስኬት መጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ እንደሚገኙ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ ተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በምርጫው ለመወዳደር የተመዘገቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምርጫው ለሀገር አንድነትና ለሕግ የበላይነት መረጋገጥ ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ እስካሁን ተሳትፏቸውን እያጠናከሩ መጥተዋል። መራጩ ሕዝብ በድምፁ የሚፈልገውን ፓርቲ ወደ ሥልጣን ለማምጣት የወሰደውን የምርጫ ካርድ በአግባቡ ይዞ፣ በምርጫው ዕለት በአግባቡ እንዲጠቀምበትም ፓርቲዎቹ መልእክት አስተላልፈዋል። የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴሃን) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ገብረመስቀል አደመ እንደገለጹት፤ ፓርቲያቸው የምርጫው ሂደት ፍትሃዊና አሳታፊ እንዲሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል። ፓርቲያቸው እስካሁን ለአባላቱና ለደጋፊዎቹ የምርጫ ሕጉንና የፓርቲውን ማኒፌስቶ መሠረት በማድረግ ግንዛቤ መፍጠሩን አውስተዋል። የሰለጠነ የፖለቲካ ትግል መገለጫው የሚፈልጉትን ፓርቲ በካርድ ወደ ሥልጣን ማምጣት መሆኑን መራጩ ሕዝብ መገንዘብ እንዳለበትም ገልጸዋል። በዚህም መራጩ ሕዝብ ያወጣውን የምርጫ ካርድ በአግባቡ በመያዝ፣ በዕለቱ ሀገርና ሕዝብን ያሻግራል ብሎ ያመነበትን ፓርቲ እንዲመርጥ መልእክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የሰሜን ኢትዮጵያ አስተባባሪና የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ሃይለማሪያም ብርሃኑ በበኩላቸው፤ በሕዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው መንግሥት ለመመስረት ምርጫ ዋናው መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል።
ካርዳችንን በጥንቃቄ በመያዝ የምንፈልገውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል -የገንዳ ውሃ ከተማና የጋዚግብላ ወረዳ ነዋሪዎች
May 23, 2026 333
ሰቆጣና ገንዳውኃ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጠቅላላ ምርጫው ለመሳተፍ የወሰድነውን ካርድ በጥንቃቄ በመያዝ ለሁሉም የሚጠቅም ፖሊሲ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በአማራ ክልል የገንዳ ውሃ ከተማና የጋዚግብላ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ። ነዋሪዎቹ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በወሰድነው ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ተጠቅመን ለህዝብና ለሀገር ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። በጠቅላላ ምርጫው ለመሳተፍ የወሰድነውን ካርድ በጥንቃቄ በመያዝ ለሁሉም የሚጠቅም ፖሊሲ ያለውን ፓርቲ እንመርጥበታለን ብለዋል። ከገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ዮሴፍ አየነው የመምረጥ መብቴን ተጠቅሜ የዜግነት ግዴታዬን ለመወጣት ተዘጋጅቻለሁ ሲሉ ተናግረዋል። ያወጣሁትን ካርድም ለህዝብ ተጠያቂ የሚሆንና ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ይገነባል ብዬ ለማምነው ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት እውን መሆን የድርሻዬን እወጣለሁ ብለዋል። ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ቤዛ አለሙ በበኩላቸው ሰላምና ዴሞክራሲን ለሚያሰፍን ፓርቲ ድምጻቸውን እንደሚሰጡ ተናግረዋል። "ካርዴን በወቅቱ ወስጃለሁ፤ በምርጫው ቀን በጠዋት ተገኝቼ ድምፄን በመስጠት ኃላፊነቴን እወጣለሁ" ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በዋግ ኽምራ ዞን የጋዝጊብላ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር ምስጋናው መኮነን ያወጡትን ካርድ አርሶ አደሩን የሚጠቅም ፖሊሲ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ እንደሚጠቀሙበት ተናግረዋል። "የምንፈልገውን ፓርቲ ለመምረጥ ሰላም ወሳኝ ነው" ያሉት አርሶ አደሩ የአካባቢያቸውን ሰላም በንቃት በመጠበቅና የመኸር እርሻ ዝግጅታቸውንም እያከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል። "የፖለቲካ ፓርቲዎች እያደረጉት ያለው ቅስቀሳ የሚበጀንን ፓርቲ ለመለየት አግዞናል" ያሉት ደግሞ ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ሞገስ ደባሽ ናቸው። ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የአካባቢያቸውን ሰላም አፅንተው እየጠበቁ መሆኑን ጠቁመው በድምፅ መስጫው ቀን ማልደው በመነሳት ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ማህበራዊ
በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት የሚደረገው ጥረት ውጤት እያመጣ ነው
May 23, 2026 239
ድሬደዋ፣ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት የሚያደርገው ጥረት ውጤት እያመጣ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። የባለ 6 ወለል ህንፃ ግንባታን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እና የኮርፖሬሽኑ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ኃይለብርሃን ዜና አስጀምረዋል። በወቅቱም የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንደገለፁት፤ ኮርፖሬሽኑ በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት የሚያደርገው ጥረት ውጤት እያመጣ ነው። ኮርፖሬሽኑ በድሬደዋ የመኖሪያ እና የንግድ ሞሎችን ተደራሽ ለማድረግ የጀመራቸው ስራዎች አበረታች በመሆናቸው ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል። የኮርፖሬሽኑ የኮርፖሬት ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኃይለብርሃን ዜና በበኩላቸው፤ ኮርፖሬሽኑ የመኖሪያ ቤት ችግርን ከመሰረቱ ለመፍታት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ውጤት እንደተመዘገበባቸው መሆኑን አመልክተዋል። ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ እየተመዘገቡ የሚገኙ የዘርፉ ለውጦችን በድሬዳዋ ለመድገም ጥናትን መሠረት ባደረገ መልኩ 13 ህንፃዎችን ለመገንባት ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በዛሬው ዕለት የተከናወነው የህንፃ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰው የኮርፖሬሽኑ 50ኛ ዓመት ምስረታ የማጠቃለያ በዓል በቀጣዩ ሰኞ በድሬዳዋ እንደሚከበርም አስታውቀዋል። ኮርፖሬሽኑ በቤቶች ልማት ዘርፍ እመርታዊ ለውጥ በማምጣት ችግሮችን በላቀ ደረጃ እየፈታ መሆኑን የገለፁት ደግሞ በኮርፖሬሽኑ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እውነቱ ወርቅነህ ናቸው። ኮርፖሬሽኑ የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት በአዲስ አበባ በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበሩን ገልፀው የዚሁ ክብረ በዓል ቀጣይ ክፍል በድሬዳዋ ከግንቦት 10/2018 ዓ/ም ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል ብለዋል። በ8 ሺህ 500 ካሬም ሜትር ስፋት ላይ የሚገነባው ዘመናዊ ህንፃ ለንግድ፣ ለመዝናኛ እና ለቢሮ አገልግሎቶች የሚውሉ የተለያዩ ክፍሎችን ያካተተ መሆኑም በስነ-ስርዓቱ ላይ ተመላክቷል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር እና ሌሎች የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና የኮርፖሬሽኑ ምክትል ስራ አስፈፃሚዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ሰው ተኮሩ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ዘርፈ-ብዙ እፎይታ እየሰጠ ነው
May 23, 2026 248
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ ሰው ተኮሩ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ዘርፈ-ብዙ እፎይታ እየሰጠ መሆኑን ተጠቃሚዎች ገለጹ፡፡ በአዲስ አበባ የተገነቡት የምገባ ማዕከላት መንግስት ለሰው ተኮር ልማት የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ያሳያሉ። ማዕከላቱ በቀን አንድ ጊዜ መመገብ የማይችሉ በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን፣ የከፋ የጤና ችግር ያለባቸውንና ጧሪ የሌላቸውን አረጋውያን በቋሚነት በየዕለቱ በመመገብ ላይ ይገኛሉ። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ቁጥር 20 የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል በቀን 500 ለሚሆኑ አቅመ ደካሞችና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ዜጎች ምገባ ያከናውናል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡት የማዕከሉ ተጠቃሚ እርቄ መኩሪያው፤ በተቋሙ አማካኝነት የዕለት ጉርሳቸውን ያለመቸገር እያገኙ መሆኑን ገልጸው፣ መንግሥት ለዜጎቹ የሚያደርገውን የሰብዓዊ ድጋፍና እንክብካቤ በእጅጉ አድንቀዋል። በአሁኑ ወቅት የምገባ ማዕከሉ በተለይም በከፍተኛ የኑሮ ውድነትና ጫና ውስጥ ለሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ትልቅ እፎይታን የሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላኛው ተጠቃሚ እናኒ ካሰይ በበኩላቸው፤ ከማዕከሉ የተመጣጠነ ምግብ እያገኙ መሆኑን ጠቅሰው፤ የከተማ አስተዳደሩ ይህንን መሰል በጎ ተግባር በማከናወኑ ሊመሰገን ይገባዋል ብለዋል። በምገባ ማዕከሉ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው መሰረት ጉታ እና የሺ ብርሃኔ የራሳቸውን ኑሮ ዘላቂ በሆነ የገቢ ምንጭ መደገፍ መጀመራቸውን ተናግረዋል። አስተያየት ሰጪዎቹ ማዕከሉ ከፈጠረላቸው የተሻለ የገቢ ዕድል ባሻገር፣ በየዕለቱ አቅመ ደካማ ወገኖቻቸውን በቅርበት ማገልገላቸው ትልቅ ሰብዓዊና የመንፈስ እርካታ እንዳጎናጸፈላቸውም ገልጸዋል። በርካታ የሥራ ፈላጊ ማኅበረሰብ ክፍሎች አዲስ ተስፋና የተረጋጋ የሕይወት መሠረት እየጣለ እንደሚገኝም አስረድተዋል። በመሆኑም መሰል ሰው ተኮር ማዕከላት መስፋፋታቸው በየአካባቢው ያለውን የሥራ አጥነት ጫና ለመቀነስና ማኅበራዊ ትስስርን ለማጠናከር ያለው ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ምሥክርነታቸውን ሰጥተዋል። የአዲስ አበባ የምገባ ኤጀንሲ ምክትል ዳይሬክተር ስንታየሁ ማሞ እንዳሉት፤ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላት ለአቅመ ደካሞች፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለወላጅ አልባ ሕፃናትና ለሀገር ባለውለታ ዜጎች አለኝታነታቸውን በተግባር እያሳዩ ነው። በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ በሚገኙ 29 የምገባ ማዕከላት ለተጠቃሚዎች ንጹህና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ እየተደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል። ይህ ሰው ተኮር ሥራ ስኬታማ ሊሆን የቻለው መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ባለሀብቶች እንዲሁም በጎ ፈቃደኛ ዜጎች ለፕሮግራሙ እያበረከቱ ባለው ቀና ድጋፍ መሆኑን አስገንዝበዋል። መርሐ-ግብሩ ወገኖችን ከመደገፍ ባለፈ፣ በኅብረተሰቡ ዘንድ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህልን እንዲሁም ማኅበራዊ መስተጋብርን በእጅጉ ያጠናከረ መሆኑንም ገልጸዋል።
እኛ ለኢትዮጵያ ብልጽግና በትጋት ስንሰራ፣ ወጣቱ የዚህ ስራ ፍሬ ተቋዳሽ ይሆናል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
May 23, 2026 230
አዲስ አበባ ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ) ፦ እኛ ለኢትዮጵያ ብልጽግና በትጋት ስንሰራ፣ ወጣቱ ደግሞ የዚህ ስራ ፍሬ ተቋዳሽ እና የሀገሪቱን ብልጽግና የሚያጣጥም ይሆናል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በአሁኑ ወቅት ሀገራቸውን የሚወዱ እና ኢትዮጵያን ከፍ ለማድረግ የሚተጉ ወጣቶችን መመልከት፣ እኛም በበለጠ ትጋት እንድንሰራ ትልቅ መነሳሳትን ይፈጥርልናል ብለዋል። " አዶናይ ብርሃነን የመሳሰሉ ወጣቶች እንደ እነ ዲላን ፔጅ ያሉ ታዋቂ የአጫጭር ማኅበራዊ ሚዲያ ዜና አቅራቢዎችን ወደ ሀገራችን በማምጣት የኢትዮጵያን በጎ ገጽታ ለመገንባት እያከናወኑት ያለው ተግባር የሚበረታታና ይበል የሚያሰኝ በመሆኑ፣ ወጣቶቹን በርቱ ልንላቸው ይገባል" ሲሉ ገልጸዋል። ትውልዱ ገብቶታል ያሉት ከንቲባዋ፣ የዛሬው የወጣቶች ድጋፍ እና ተነሳሽነት እጅግ አስደናቂ ነበር ብለዋል።
የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን ከጥፋት መንገድ በመውጣት የሰላምና የልማት ዘብ ለመሆን ተዘጋጅተናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
May 23, 2026 205
ጎሊና፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን ከጥፋት መንገድ በመውጣት የሰላምና ልማት ዘብ ለመሆን ተዘጋጅተናል ሲሉ በአፋር ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በአፋር ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት የቀድሞ ታጣቂዎች፤ በፈንቲ ረሱ ዞን ጎሊና ወረዳ በሚገኘው የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የአፋር ጊዜያዊ ዲሞብላይዜሽን ማዕከል ሲከታተሉ የነበረውን የተሃድሶ ሥልጠና አጠናቀዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አሰከር ኖራ፤ በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት የአካባቢውን ሕዝብ መበደሉን አስታውሶ በጥፋቱ በመጸጸት ለመካስ መዘጋጀቱን ተናግሯል። በሥልጠና ቆይታው የልማት አርበኛ እና የሰላም ዘብ ለመሆን ብዙ የተማረበትና ለተግባራዊነቱ ቃል መግባቱን ገልጿል። ሌሎች በተሳሳተ መንገድ የሚንቀሳቀሱ ወጣቶችም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ሰልጥነው ማኅበረሰቡን መቀላቀል እንዳለባቸው አስገንዝቧል። ሌላኛው የቀድሞ ታጣቂ ከሊል ሙስጠፋ እና መዲና አህመድ፤ በተሳሳተ መንገድ በመመራት እና በመሳተፍ የራስን ወገን ከመበደል በስተቀር የሚመጣ ለውጥ የሌለ መሆኑን አረጋግጠናል ብለዋል። በመሆኑም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን መጥተናል ሀገራችንንና ሕዝባችንንም ለማገልገል ተዘጋጅተናል ነው ያሉት። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፤ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የቀድሞ ታጣቂዎችን በማሰልጠን ወደ ሕብረተሰቡ እንዲቀላቀሉና መልሰው እንዲቋቋሙ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። በዚህም መሠረት በአፋር ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩት የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን በመቀበል፣ ከስህተታቸው ተምረው የሰላም ኃይልና የልማት አጋዥ ለመሆን ዝግጁ መሆናቸውን አንስተው ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲገቡ አሳስበዋል። የአፋር ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አብዱ ሙሳ፤ የቀድሞ ታጣቂዎቹ የሰላም ጥሪን ተቀብለው የተሃድሶ ሥልጠና መውሰዳቸው ለሰላም ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ያሳዩበት ነው ብለዋል። በመሆኑም በቀጣይ የሰላምና የልማት አጋሮች ለመሆን መዘጋጀታቸውን ጠቁመው በዘላቂነት እንዲቋቋሙ ድጋፍ እንደማይለያቸው ተናግረዋል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የሚወስን ቁልፍ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ነው
May 23, 2026 391
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሀገርን ኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የሚወስን ቁልፍ የብሔራዊ ጥቅምና የሕልውና ጉዳይ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ገለጹ። ጥያቄው ታሪካዊነትን ከመልክዓ-ምድራዊነት፣ ሕጋዊነትን ደግሞ ከፍትሐዊ ተጠቃሚነት ጋር ያሰናሰለ ጠንካራና ምክንያታዊ መሠረት ያለው መሆኑን አስገንዝበዋል። ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያና የቀይ ባሕር ዳርቻ ትስስር በሀገረ-መንግሥት ምሥረታና ግንባታ ታሪክ ውስጥ እጅግ የጠበቀ ነው ብለዋል፡፡ ለአብነትም በአክሱም ሥልጣኔ ዘመን የነበረው ኃያልነትና በአዱሊስ ወደብ አማካኝነት ከመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች ጋር የተደረገው ሰፊ የንግድ ልውውጥ ከቀይ ባሕር ቁርኝት የመነጨ እንደነበር አብራርተዋል። በታሪክ ሂደት ውስጥ ኢትዮጵያን ከቀይ ባሕር ለማራቅ የውስጥ ባንዳዎችን በማሰለፍ ጭምር የሸረቡት ሴራና የተሳሳተ ስሌት በእጅጉ የሚያስቆጭ የታሪክ ስብራት መሆኑን ጠቁመዋል። ዛሬም ቢሆን የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ለማደናቀፍ የውጭ ኃይሎችና የእነርሱ ተላላኪ የሆኑ የሀገር ውስጥ ኃይሎች በተሳሳተ ስሌት እየተጓዙ መሆኑን አክለዋል። ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት የባሕር በር ጉዳይን ማንሳት እንደ ተንኳሽነት የሚቆጠርበትን አደገኛ ትርክት በመስበር፣ ወሳኝ የምክክርና የንግግር አውድ እንዲፈጠር መደረጉን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ይፋ ካደርጉበት ጊዜ ጀምሮም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በህዝብ ለህዝብ ግንኙነትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ሥራዎች ማከናወኑን አስታውሰዋል። ኢትዮጵያውያን በብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ላይ የተደመረ ዕይታና ፅኑ አቋም ሊኖራቸው ይገባል ብለዋል። በምንም ዓይነት የፖለቲካ ልዩነት የትውልድን ጥያቄ አሳልፎ መስጠት እንደማይገባና ለብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት መከበር በትብብር መቆም እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎቷን በሰላማዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ እያቀረበች መሆኑን በመጥቀስ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ቦሊቪያና ፔሩ፣ ብራዚልና ፓራጓይ፤ በአፍሪካ የማሊ፣ ሴኔጋልና ኮትዲቯር የተጠቀሙባቸውን የጋራ መፍትሔዎች በተሞክሮነት አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 መሠረት የኢኮኖሚ ውህደት የሰፈነባት አህጉር ለመፍጠር በቀጣናው ሀገሮች መካከል የኃይል ትስስር በመፍጠር የባሕር በር ፍላጎቷን በሰፊው እያስረዳች መሆኑንም ገልጸዋል። የባሕር በር አለመኖር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በየዓመቱም ኢትዮጵያ ለወደብና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ብቻ ከአንድ ነጥብ አምስት እስከ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ወጪ ለማድረግ መገደዷን ተናግረዋል። ይህም በወጪና ገቢ ንግድ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲሁም በጠቅላላው የዕድገት ጉዞ ላይ ትልቅ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን አስገንዝበዋል። በመሆኑም መገናኛ ብዙኃን ብሔራዊ መግባባትን በማጉላት፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ማስረዳት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን በማስከበር ዕድገትና ብልፅግና ከሚወስኑ ቁልፍ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ነው ብለዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የተገነባውን የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል መረቁ
May 23, 2026 253
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሚገኘውን የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመልዕክታቸው፤ የተቀናጀ የከተማ የግብርና ማዕከሉ በ3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ እና 18 ሱቆችን እንዲሁም 18 ሼዶችን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል። አዲስ አበባ ለሁሉም የምትመች የጋራ ቤትና ልማቷም አካታች መሆኑን አመልክተዋል። ባለፈው ሥርዓት አርሶ አደሩ የሚገፋበት፣ መሬቱ ብቻ ተፈልጎ እርሱ የሚዘነጋበት የነበረ በመሆኑ ለለውጡ መምጣት ገፊ ምክንያት እንደነበር አስታውሰዋል። የአሁኑ የከተማ አስተዳደር አርሶ አደሩን በሁሉም የከተማ ልማት ውስጥ አካቶ አብሮ እንዲለማ እና ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ እያደረገ መሆኑን ከንቲባ አዳነች ገልጸዋል። አርሶ አደሩ ለልማት በሚነሳበት ወቅት ተገቢውን ካሳ ከማግኘት ባለፈ ከልማቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ ቀደም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በ14 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተገነባው የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ልህቀት ማዕከል እና ዛሬ በለሚ ኩራ የተመረቀው ማዕከል የዚሁ ማሳያ መሆናቸውንም ነው ያብራሩት። እነዚህን መሰል ማዕከላት የከተማው ነዋሪ የሚያጋጥመውን የዋጋ ንረት ለመከላከል እና በተመጣጣኝ ዋጋ የግብርና ምርቶችን ለማቅረብ ያስችላሉ ያሉት ከንቲባዋ፣ አሰራሩ በጋራ ማደግንና ተባብሮ መበልጸግን የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይህንን ግዙፍ ስራ በማቀድ፣ በማስተባበርና ውጤታማ እንዲሆን በማድረግ ረገድ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በካፋ ዞን የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት አሳድገዋል
May 23, 2026 158
ቦንጋ ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦በካፋ ዞን ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደጋቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በካፋ ዞን ሺሾእንዴ ወረዳ ከ44 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ወጪ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል። ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል ሞዴል ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት፣ የወሺ ፏፏቴ የቱሪስት መዳረሻ፣ ሞዴል ጤና ኬላ እንዲሁም የኖባ ሽመሮ እና ወሺ ጊዳ የመንገድ መሰረተ ልማት ይጠቀሳሉ። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ እንደገለፁት፤ በዞኑ የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት አሳድገዋል። ዛሬ የተመረቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶችም የዚሁ ማሳያዎች ናቸው ያሉት አቶ እንዳሻው፣ በዞኑ በዚህ ዓመት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ለመቅረፍ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በትምህርቱ ዘርፍ የሚስተዋለውን የጥራትና ውጤታማነት ችግር ለመፍታትም ሞዴል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የጤና አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረግ ትኩረት የተሰጠው አንዱ ተግባር ነው ያሉት አስተዳዳሪው በዚህም የጤና ተቋማትን ከመገንባት ባለፈ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተሰራው ስራ ውጤት ማስመዝገቡን ነው የተናገሩት፡፡ የቱሪስት መዳረሻን በማልማት ረገድ ለወጣቶች ስራ ዕድል በመፍጠርና ቱሪስቶችን ለመሳብ በተደረገው ጥረት ዛሬ የተመረቀው የወሺ ፏፏቴ መዳረሻም የተደበቀውን እምቅ ሀብት አጉልቶ ያወጣ ነው ብለዋል። የሺሾእንዴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደምሴ ገብረማርያም በበኩላቸው፣ በወረዳው የህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለሆኑ የመንገድ፣ የትምህርት፣ የጤናና ሌሎች መሰረተ ልማት ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በዛሬው እለት የተመረቁት መንገዶች አርሶ አደሩ ምርቱን ለገበያ እንዲያወጣ እንዲሁም በፍጥነት የጤና አገልግሎትን እንዲያገኝ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው ነው ብለዋል፡፡ የወረዳው ነዋሪዎችም ከዚህ ቀደም በአካባቢያቸው መንገድ ባለመኖሩ ምርታቸውን ወደ ገበያ ለማውጣትም ሆነ ወደ ጤና ተቋማት ፈጥኖ ለመድረስ ይቸገሩ እንደነበር ተናግረዋል። ዛሬ የተመረቁት የትምህርት፣ የመንገድና የጤና ተቋማት ለበርካታ ዓመታት ይነሱ የነበሩ ጥያቄዎችን የመለሱ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በኦሮሚያ ክልል በለውጡ አመታት በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ከ43ሺህ በላይ ደርሰዋል -ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ
May 23, 2026 259
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ከለውጡ በፊት ከ10ሺህ በታች የነበረው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በለውጡ አመታት በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ከ43ሺህ በላይ መድረሳቸውን የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካን መርቀዋል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የኦሮሚያ ክልልን የኢንቨስትመንት ማዕከል ለማድረግና የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሞተር እንዲሆን በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የመደመር እሳቤን መሠረት በማድረግ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ሰፊ ሥራ መሠራቱንም ገልጸዋል። በክልሉ ቡልቡላ እና ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የነቀምቴ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን እንዲሁም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ግንባታው የተጀመረውን ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በዋቢነት አንስተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ብቻ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ባለሃብቶች ወደ ኢንቨስትመንት ለመግባት በሂደት ላይ እንደሚገኙ እና ከ30 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ደርሰዋል ብለዋል። የክልሉ መንግሥት ቢሮክራሲን በመቀነስ፣ አሠራሮችን በማሳለጥ፣ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት እና ወጣቶች ክህሎት ይዘው የልማቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን እየፈጠረ መሆኑንም አስታውቀዋል። የዛሬው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ምረቃም የዚሁ እንቅስቃሴ ውጤት አካል መሆኑን ነው የገለጹት። የግብርናው ዘርፍም ከተለመደው አሠራር ወጥቶ ወደ ኢንቨስትመንት እየተሸጋገረ መሆኑን ጠቁመው፣ በተያዘው መንገድ በቁርጠኝነት ከተሠራ የክልሉም ሆነ የሀገሪቱ ብልጽግና በአጭር ጊዜ እውን እንደሚሆን ተናግረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የአፈር ለምነትን በዘላቂነት የሚጠብቁ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮች እየተጠናከሩ ነው
May 23, 2026 210
አምቦ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ የአፈር ለምነትን በዘላቂነት የሚጠብቁ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን በመተግበር ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል አዲስ በአፈርና ውሃ ላይ ጥናትና ምርምር ለማድረግ የሚያግዝ ላብራቶሪ ስራ አስጀምሯል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ንጉሤ ደቻሳ (ፕ/ር) እንደገለጹት፤ የአፈር ለምነትን መጠበቅ ለምርትና ምርታማነት እድገት መሰረታዊ በመሆኑ፣ የአፈር ለምነትን የሚቀንሱ ችግሮችን በሳይንሳዊ ዘዴ መለየትና የላብራቶሪ ማዕከላትን ማጠናከር አስፈልጓል። በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ዛሬ ተመርቆ ስራ የጀመረው የአፈር እና ውሃ ላብራቶሪም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የላብራቶሪው ዋና ዓላማም የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማድረግና የግብርናውን ዘርፍ ማሳደግ እንደሆነ አንስተዋል። የአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ጀማል ቶላ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ባለፉት ዓመታት ከአካባቢው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ለእጽዋት ጥበቃ የሚውሉ ሳይንሳዊ የምርምር ውጤቶችን ሲያቀርብ መቆየቱን ተናግረዋል። የምርት መጠንን ለመጨመር የሰብል ልማትን የሚደግፉ ሰፋፊ የግብርና ምርምሮች እየተካሄዱ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ይህም የአካባቢውን አርሶ አደሮች ከመደገፍ ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ-ብዙ ስራዎች እንዲከናወኑ ማድረጉን ተናግረዋል። ማዕከሉ ግብርናን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችንና የግብርና ግብዓቶችን በማቅረብ የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። የአምቦ ወረዳ አርሶ አደር ወይዘሮ እሸቱዋ ሚደቅሳ በበኩላቸው፤ ከግብርና ማዕከሉ ባገኙት ስልጠና በመታገዝ የተሻሻለ የበቆሎ ዝርያ ወስደው በመዝራታቸው፣ ምርታቸው ከበፊቱ እጥፍ መጨመሩን ተናግረዋል።
የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በክህሎት የበለፀገ የሰው ኃይል በማፍራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን እያሳለጠ ነው
May 23, 2026 256
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በክህሎት የበለፀገ የሰው ኃይል በማፍራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን እያሳለጠ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብር እስከ አሁን ከ4 ነጥብ 85 ሚሊየን በላይ ሰዎች ስልጠና በመውሰድ የሰርተፍኬት ባለቤት እየሆኑ እንደሚገኝም አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ስልጠናን ሐምሌ 2016 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው የሚታወስ ነው። የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ተነሳሽነት ወጣቶች ላይ ትልቅ ለውጥ ለማምጣት ያለመ የዲጂታል ክህሎት ማልሚያ መርሃ ግብር ሆኖ እያገለገለ ሲሆን በዚህም ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገብ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግሥት ጋር በመተባበር ያስጀመረው የኢትዮ-የኮደርስ ስልጠናም ሀገራዊ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን በማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። ስልጠናውም ዜጎች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ዳታ አናሊሲስ፣ በአንድሮይድና በፕሮግራሚንግ ዴቨሎፕመንት ዋና ዋና ዘርፎች ስልጠና የሚያገኙበትን ምኅዳር ፈጥሯል። ስልጠናው በኦላይን ሥርዓት በነፃ የሚሰጥና ዜጎች ያለ ዕድሜ ገደብ መሠረታዊ የዲጂታል ስልጠና ወሰደው ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው ሰርተፍኬት ያገኙበታል። የዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓትን በመገንባት ሂደትም በርካታ ዜጎችን የቴክኖሎጂ ክህሎት በማስታጠቅ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል። ይህም የኢትዮጵያን የግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ብዝኅ የኢኮኖሚ ጉዞ የሚያሳልጥ ሀገር በቀል የዲጂታል ክህሎት የታጠቀ ትውልድ በማፍራት እያስቻለ ነው። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ስዩም መንገሻ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዲጂታል ኢኮኖሚን መገንባት የሚያስችል ሥነ-ምኅዳር ተፈጥሯል። ለአብነትም የአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በርካታ ዜጎች የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የሚታጠቁበትን አስቻይ የአሰራር ሁኔታ መፍጠሩን አስታውቀዋል። የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ከተጀመረ አንስቶም እስካሁን ከ4 ነጥብ 85 ሚሊየን በላይ ዜጎች የስልጠናው አካል በመሆን የተለያዩ የዓለም አቀፍ ሰርተፊኬት ባለቤት እየሆኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለፈጠራና ቴክኖሎጂ ልማት የተሰጠው ትኩረትም የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያሳልጥ የሰው ሃይል ማፍራት እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠናም የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የታጠቀ ብቁ የሰው ሃይል በማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አንስተዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩም ዜጎች ባሉበት ቦታ ሆነው በኦላይን ሥርዓት ዕውቀት የሚሸምቱበትን ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል። በቀሪ የሥልጠናው ጊዜያትም ዜጎች የዕድሉ ተጠቃሚ በመሆን የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት ማዳበር እንደሚችሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በማረጋገጥ የሳይበር ደኅንነት ስጋትን የሚቀለብስ የሰው ሃይል ማፍራት እየተቻለ ነው
May 21, 2026 797
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በማረጋገጥ የሳይበር ደኅንነት ስጋትን የሚቀለብስ የሰው ሃይል ማፍራት እየተቻለ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ገለጸ። አስተዳደሩ በዘንድሮው ክረምት ለ5ኛ ጊዜ የሚያካሂደውን የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ (Cyber Talent Summer Camp) ዝግጅት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። የአስተዳደሩ የሳይበር ልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር ቢሻው በየነ በመግለጫቸው፤ መርሃ ግብሩ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች በማሰልጠን የሳይበር ደኅንነትና የቴክኖሎጂ ሙያተኞችን ለማፍራት ያለመ ነው ብለዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያን የሳይበር ደኅንነትና ሉዓላዊነት የማስጠበቅ አቅምን የበለጠ ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ ኢትዮጵያ በዘርፉ ሀገራቸውን ከሳይበር ጥቃት የሚከላከልና ብቁ የሳይበር ሠራዊት ማፍራት መሆኑን አብራርተዋል። እንደ እስራኤል፣ እንግሊዝ እና አሜሪካ ያሉ ሀገራት ተሞክሮ መርሀግብሩ ታዳጊዎችን ለማፍራት ያለውን ወሳኝነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። ይህ ካምፕ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግና የኢትዮጵያን ዲጂታል ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። የዘንድሮው የስልጠና ካምፕ በክልል ደረጃ በስድስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲካሄድ የተወሰነ ሲሆን ይህም ታዳጊዎች በቅርበት ስልጠናውን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል። በእስካሁኑ ሂደትም ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ከ4 ሺህ በላይ ታዳጊዎችና ወጣቶች መመዝገባቸውን ገልፀዋል። ምዝገባውም ግንቦት 17/2018 ዓ.ም የሚጠናቀቅ በመሆኑ በሳይበር ደህንነትና ቴክኖሎጂ ልዩ ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎችና ወጣቶች በኦንላይን እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
የምርት ጥራት ደረጃ ማረጋገጫ መተግበሪያው የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው
May 21, 2026 473
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ የምርት ጥራት ደረጃ ማረጋገጫ መተግበሪያው የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት አፈጻጸም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በዛሬው ዕለት የምርት ጥራት ደረጃን በኦንላይን ማረጋገጥ የሚያስችል መተግበሪያ አስመርቆ ወደ ስራ አስገብቷል። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሠረት በቀለ (ዶ/ር) ተገኝተዋል፡፡ ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርሙ በንግድ ስርዓቱ ላይ ትልቅ እመርታ እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከ46 በላይ አገልግሎቶች በኦንላይን እየተሰጡ እንደሚገኙ ጠቅሰው፥ ይህም የንግድ ሥርዓቱን በማዘመን የምርት ጥራት አፈፃጸም ላይ የላቀ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት አስር ወራት ብቻ ከወጪ ንግድ ከ8 ነጥብ 7 ቢሊየን በላይ የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱንም ነው የተናገሩት፡፡ ዛሬ የተመረቀው የኦንላይን መተግበሪያ አገልግሎቶችንና የምርት ጥራትን በላቀ አፈፃጸም መምራት የሚያስችል መሆኑንና የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት አፈፃጸም ውጤታማነት ለማላቅ አይነተኛ ሚና ያበረክታል ብለዋል። የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሠረት በቀለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ተስፋ ሰጭ የለውጥ ጉዞ እያስመዘገበች ትገኛለች ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ የለውጥ ጉዞውን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሕግና ተቋማዊ ማሻሻያዎችን እንዳደረገ በመግለጽ፡፡ የዚህ ጥረት አካል የሆነው የኦንላይን የምርት ጥራት ማረጋገጫ መተግበሪያ የኢትዮጵያ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ በዋጋና በጥራት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑንም አክለዋል፡፡ መተግበሪያው የኢንስቲትዩቱን የማስፈጸም አቅም ሀገሪቱ ከደረሰችበት የዕድገት ደረጃ ጋር እንዲጣጣም አጋዥ ስለመሆኑም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በምርት ጥራት ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ እንደሚሆኑ የተናገሩት ደግሞ የአፍሪካ የደረጃዎች ተቋማት የማዕከላዊ ኮሚቴ ጸሐፊ ሬዩበን ጊሶር ናቸው፡፡ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወናቸውን አጠቃላይ ተቋማዊ የሪፎርም ስራዎችን አስመርቋል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማለፍ አልቻለም
May 23, 2026 296
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ ከ17 ዓመት በታች ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ በተደረገ የመለያ ጨዋታ ሞዛምቢክ ኢትዮጵያን በመለያ ምት አሸንፋለች። በመሐመድ ስድስተኛ ስፖርት ኮምፕሌክስ በተካሄደው ጨዋታ አሚር ሚስባህ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ጎል ኢትዮጵያን መሪ አድርጓል። ዲዬጎ ፔሌምቤ በ57ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ባሳረፋት ጎል ሞዛምቢክ አቻ ሆናለች። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት በመጠናቀቁ ወደ መለያ ምት አምርቷል። በመለያ ምቱም ሞዛምቢክ 5 ለ 4 በማሸነፍ በኳታር አስተናጋጅነት ለሚከናወነው 21ኛው ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ ማለፏን አረጋግጣለች። እንየው ስለሺ ከኢትዮጵያ በኩል ፍጹም ቅጣት ምቱን የሳተ ተጫዋች ነው። በአሜሪካዊው አሰልጣኝ ቤንጃሚን ዚመር የሚመራው ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማለፍ አልቻለም። በሌላኛው የመለያ መርሐ ግብር ጋና ከዩጋንዳ ምሽት አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አዘጋጇ ሞሮኮ፣ ግብጽ፣ ኮትዲቯር፣ ካሜሮን፣ ታንዛንያ፣ ማሊ፣ ሴኔጋል እና አልጄሪያ በቀጥታ ወደ ዓለም ዋንጫ ያለፉ ሀገራት ናቸው። 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ እስከ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። በአፍሪካ ዋንጫው እየተሳተፉ ካሉ 16 ሀገራት መካከል 10ሩ በጥቅምት እና ህዳር ወር 2019 ዓ.ም በኳታር ለሚካሄደው 20ኛው የፊፋ ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ተሳታፊ ይሆናሉ። በዓለም ዋንጫው ላይ 48 ሀገራት ይሳተፋሉ።
ሁል ሲቲ ከዘጠኝ ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ተመለሰ
May 23, 2026 232
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ሻምፒዮምሺፕ የጥሎ ማለፍ የፍጻሜ ጨዋታ ሁል ሲቲ ሚድልስቦሮውን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በዌምብሌይ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኦሊ ማክበርኒ በ94ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በጨዋታው ሚድልስቦሮው ብልጫ ቢውስድም ሁል ሲቲ በባከነ ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፈው ግብ አሸናፊ አድርጎታል። ውጤቱን ተከትሎ ሁል ሲቲ ከዘጠኝ ዓመታት በኋላ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መመለሱን አረጋግጧል። ክለቡ ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ ላይ የተወዳደረው እ.አ.አ 2016/17 ነበር። ሚድልስቦሮው ከዘጠኝ ዓመታት በኋላ ወደ ሊጉ የመመለስ ህልሙ ሳይሳካ ቀርቷል። ኮቨንተሪ ሲቲ እና ኢፕስዊች ታውን አስቀድመው ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ማደጋቸውን ያረጋገጡ ክለቦች ናቸው።
በድሬዳዋ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታ የፈጠሩ ናቸው
May 23, 2026 159
ድሬዳዋ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦በድሬዳዋ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታ የፈጠሩ መሆናቸውን የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካል የሆነ አመራሮች፣ የአባላትና ደጋፊዎች የተሳተፉበት የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሂዷል። በመርሐግብሩ ላይ የተሳተፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ እንደገለጹት፤ ስፖርት ጤናማ፣ ተወዳዳሪ እና አሸናፊ ትውልድ ለማፍራት መሠረታዊ ጉዳይ በመሆኑ፤ በአስተዳደሩ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በጥራትና በፍትሐዊነት በገጠርና በከተማ እንዲገነቡ ተደርጓል። ወጣቶች የነገ ብሩህ ሕይወታቸው ፍሬያማ እንዲሆን በየወረዳው የወጣቶች ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጉንም ገልጸዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በአስተዳደሩ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታ የፈጠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ፓርቲው የሕዝብን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ፕሮጀክቶችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በድሬዳዋ ገጠርና ከተማ ውጤታማ እና ጤናማ ትውልድ ለማፍራት ለስፖርት ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት፣ ተወዳዳሪ ትውልድ በመፍጠር ረገድ ወደር የሌለው ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል። በአስተዳደሩ እየተመዘገቡ የሚገኙ ውጤቶችም ሆኑ እንደ ሀገር እየተከናወኑ የሚገኙ አሻጋሪ ፕሮጀክቶች፣ የኢትዮጵያን ከፍታ ለማረጋገጥ የተጀመረውን ጉዞ ዕውን የሚያደርጉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ብሩኖ ፈርናንዴዝ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ
May 23, 2026 198
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ የማንቸስተር ዩናይትድ አምበል ብሩኖ ፈርናንዴዝ የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች (Player of the Season) በመሆን መመረጡን የሊጉ አስተዳደር ይፋ አደረገ። የፕሪሚየር ሊጉ አስተዳደር እንደገለጸው፣ የ31 ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጫዋች የዓመቱ ምርጥ ተብሎ የተመረጠው በውድድር ዓመቱ ባሳየው የጎል ዕድሎችን የመፍጠር ብቃትና ለቡድኑ ስኬት ላበረከተው አስተዋጽኦ ነው። ማንቸስተር ዩናይትድ በውድድር ዘመኑ አጋማሽ ላይ በነበረበት የአሰልጣኝ ቅያሬና መዋዠቅ ውስጥ አልፎ በጊዜያዊና በቋሚ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ መሪነት በደረጃ ሰንጠረዡ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ እንዲሁም ወደ አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ እንዲመለስ ተጫዋቹ የነበረው ሚና የጎላ እንደነበር ተመላክቷል። ፖርቱጋላዊው አማካይ በውድድር ዓመቱ ስምንት ጎሎችን ማስቆጠር የቻለ ሲሆን፥ በተጨማሪም 20 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን ለቡድን አጋሮቹ በማቀበል የሊጉን ክብረ ወሰን መጋራት ችሏል። ከዚህ ቀደም ቲዬሪ ሄነሪ (በአርሰናል) እና ኬቨን ደ ብሮይን (በማንችስተር ሲቲ) በነበሩበት ወቅት በተመሳሳይ 20 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አቀብሏል። ፓርቹጋላዊው አማካይ ቡድኑ ነገ ከብራይተን ጋር በሚያደርገው የመጨረሻ ጨዋታ ላይ ክብረ ወሰኑን ብቻውን የመያዝ ዕድል አለው። በተጨማሪም ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዘንድሮው የውድድር ዓመት 132 የግብ ዕድሎችን በመፍጠር የበላይነቱን የያዘ ሲሆን፥ በዚህ ረገድ የሊቨርፑሉ ዶሚኒክ ሶቦስላይ በ89 የጎል ዕድሎች ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ማንቸስተር ዩናይትድ ይህንን የፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ክብር ሲያገኝ ከ15 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፥ የመጨረሻው ሽልማት የተመዘገበው እ.አ.አ በ2010/11 የውድድር ዘመን በሰርቢያዊው ተከላካይ ኔማንያ ቪዲች አማካኝነት እንደነበር ይታወሳል። ፈርናንዴዝ ይህንን ሽልማት ያሸነፈው ከእግር ኳስ ባለሙያዎች፣ ከሊጉ አምበሎችና ከደጋፊዎች በተሰበሰበ ድምፅ ሲሆን፤ ሽልማቱን ለማግኘት ከቀረቡት መካከል ዘንድሮ የሊጉን ዋንጫ ያነሱት የአርሰናል ተጫዋቾች ዴክላን ራይስ፣ ጋብርኤል ማጋሌሽ፣ ዴቪድ ራያ እንዲሁም የማንቸስተር ሲቲውን አርሊንግ ሃላንድ እና አንቶዋን ሴሜኒዮ፣ የኖቲንግሃም ፎረስቱን ሞርጋን ጊብስ-ዋይት እና የሬንትፎርዱን ኢጎር ቲያጎ በብልጫ ማሸነፍ ችሏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ተጫዋቹ ከቀናት በፊት በፈረንሳይና በእንግሊዝ የእግር ኳስ ጸሐፊዎች ማኅበር (FWA) የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ መመረጡ የሚታወስ ሲሆን፥ የክለቡም የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አግኝቷል። በተያያዘም የማንቸስተር ሲቲው የ21 ዓመት አማካይ ኒኮ ኦራይሊ የሊጉ የዓመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች በመባል ተመርጧል።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለቀጣናው ብልፅግና የላቀ ሚና አለው
May 23, 2026 230
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር እንዲሁም ብልፅግናን ለማጎልበት የላቀ ሚና እንዳለው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የራሷን የተፈጥሮ ሀብት ከመንከባከብ ባለፈ፣ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚከሰቱ አደጋዎችን በጋራ ለመከላከል የአካባቢውን አገራት አብሮ የመልማት ዕቅድ ይዛ እየሠራች ስለመሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህም በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለጎረቤት አገራት በርካታ ችግኞችን ማበርከቷ ይታወቃል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚከሰቱ የተፈጥሮ መዛባቶችን ለመከላከል፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና አካባቢን ለመታደግ ታስቦ በከፍተኛ ሀገራዊ ቁርጠኝነት እየተተገበረ የሚገኝ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው። ይህ ንቅናቄ በአገር ውስጥ ካስገኛቸው ሁለንተናዊ ጥቅሞች ባሻገር፣ ለጎረቤት አገራትና ለጠቅላላው የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ የምታከናውነው የተፈጥሮ ጥበቃ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለቀጣናው አገሮች የሚተርፍ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ነው፡፡ የኢጋድ ሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በቀጣናው እንደ ጎርፍ፣ የበረሃ አንበጣ እና ድርቅ ያሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎች የሰዎችን መፈናቀልና ስደት ይፈጥራሉ፡፡ በዚህም ዜጎች ከአካባቢያቸው ችግሩ ወደ ሌለባቸው አካባቢዎችና ድንበሮችን አቋርጠው የሚሰደዱበትን ሁኔታ የሚፈጠር ሲሆን፤ ይህም በቀጣናው ላይ የሚያሳድረው ጫና ቀላል እንዳልሆነ አመልክተዋል። ይህንን ተግዳሮት ለመቋቋም በኢትዮጵያ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ውጤቶችን እያሳየ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ አሁን ላይ የሚታየው መደበኛ የዝናብ ሁኔታ ስኬት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ተከትሎ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እየተጠናከረ በሄደ ቁጥር በቀጣናው የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር፣ ሰላምና ብልፅግናን ለማጎልበት የራሱ የሆነ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው አንስተዋል። ይህንን የኢትዮጵያን መልካም ተሞክሮ በመረዳት እንደ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ጅቡቲ ያሉ የጎረቤት አገራት ተመሳሳይ አረንጓዴ ልማቶችን እየተከተሉ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ከዋና ዋና ዓላማዎቹ መካከል አንዱ የግብርና እና የአካባቢ ጥበቃ ልማት መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ ይህንን የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ሀሳብ በጽኑ እንደሚደግፈው ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ባለፉት ዓመታት በከፍተኛ ተነሳሽነት ሲተገበር ቆይቷል። በመርሀግብሩ እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ጉልህ ድርሻ እየተጫወተ ይገኛል። ይህ ግዙፍ ብሔራዊ የልማት ፕሮጀክት በኅብረተሰቡ ዘንድ ችግኞችን የመትከልና የመንከባከብ በጎ ባህል እንዲዳብርና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ እንዲያድግ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል። በተለይም በችግኝ ማፍላት፣ በተከላና ተያያዥ ሥራዎች ላይ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር በሀገሪቱ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ላይ አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎችን ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ
May 22, 2026 653
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 14/2018 (ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎችን ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች በርካታ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ ስፍራዎች ላይ ለዝናብ መፈጠር አመቺ የሆኑ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች አንጻራዊ ጥንካሬ ይኖራቸዋል። ከእርጥበት አዘል የአየር ሁኔታው ጋር ተያይዞም የተሻለ የዝናብ ስርጭት እንደሚኖር ገልጿል። በዚህም በደቡብ፣ በምዕራብ፣ በደቡብ ምዕራብ፣ በደቡብ ምስራቅ፣ በምስራቅ እንዲሁም በስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች የተሻለ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚኖር አመልክቷል። በሚቀጥሉት ቀናት ከሚኖሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በመነሳት፤ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎችን ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ብዙ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ ብሏል። አልፎ አልፎ በውኃ አካላትና በአካባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በመነሳት፤ በጥቂት የደቡብ፣ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች መጠቆማቸውን ገልጿል። ይህም ለግብርና ሥራ በቂ የአፈር ውስጥ እርጥበት እንዲኖር በማድረግ ለሰብሎች፣ ለግጦሽ ሳርና ለመጠጥ ውኃ አቅርቦት አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዳለው አስታውቋል። ከተፈጥሮና ሰው ሠራሽ የውኃ ማጠራቀሚያዎችን አቅም ለማሳደግ እንዲሁም ለቋሚ ተክሎችም አዎንታዊ ሚና እንዳለው ገልጿል። በተጨማሪም ለመኸር ሰብሎች የማሳ ዝግጅትና ዘር ለመዝራት፣ ፍሬ በማፍራትና በተለያየ የእድገት ደረጃ ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎች የውኃ ፍላጎት መሟላት፣ ለአረንጓዴ ዕፅዋት ልምላሜ፣ ለመጠጥ ውኃና ለግጦሽ ሳር አቅርቦት መሻሻል የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ተጠቁሟል። በተፋሰሶች ላይ ያለውን የእርጥበት ሁኔታ በተመለከተም ባሮ አኮቦ፣ መካከለኛና ታችኛው አባይ፣ በአብዛኛው ኦሞ ጊቤ፣ በላይኛውና መካከለኛው ስምጥ ሸለቆ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ የገጸ ምድር ውኃ ፍሰት ይኖራቸዋል ብሏል። በላይኛው ገናሌ ዳዋ፣ ኦጋዴን፣ ታችኛው ተከዜ እንዲሁም በላይኛውና መካከለኛው ዋቤ ሸበሌ ደግሞ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር ውኃ ፍሰት እንደሚያገኙ ይጠበቃል ብሏል። በተጨማሪም ደረቅ የገጸ ምድር ውኃ ፍሰት የሚኖራቸው በአብዛኛው አፋር ደናኪል፣ አይሻ፣ መካከለኛና ታችኛው አዋሽ እንዲሁም በታችኛው ገናሌ ዳዋ መሆኑን የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ ሲል ገልጿል። በሌላ በኩል በበልግ ወቅት የሚኖረው የሙቀት መጠን መጨመርና በሌሊት ደግሞ የሚታየው ወበቅ አንዱ የዚህ ወቅት ክስተት መሆኑን ጠቁሟል። ከሚኖረው ከፍተኛ የፀሐይ ኃይል ጋር ተያይዞም በተለይም በጋምቤላ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል-ጉሙዝና በምዕራብ አማራ አካባቢዎች ላይ የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት ከ32 እስከ 41 ዲግሪ ሴልሺየስ እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል።
በክልሉ ከ261 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ ችግኞችን ለመትከል የ ጉድጓድ ቁፋሮ ስራ ተጀምሯል
May 20, 2026 901
ባህርዳር ፤ግንቦት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከ261 ሺህ ሔክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ ችግኞችን ለመትከል የጉድጓድ ቁፋሮ ስራ መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንደገለፁት የክልሉን የደን ሽፋን ቀድሞ ወደ ነበረበት ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ነው። በመጭው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ የዋንዛ፣ ወይራ ፣ ዝግባ ፣ ፅድ ፣ አኬሺያ ዲከረንስ፣ ባህር ዛፍ፣ የፍራፍሬና ሌሎች ችግኞችን ለመትከል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የችግኝ ተከላውን በስኬት ለማከናወን እስካሁን 401 ሚሊዮን በላይ ጉድጓዶችን በማስቆፈር ለተከላ ዝግጁ ማድረግ መቻሉን አረጋግጠዋል። በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ ግብን ለማሳካት ተጨማሪ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶችን የማስቆፈር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። ባጠቃላይ በክረምቱ ለሚካሄደው ችግኝ ተከላ 261 ሺህ 297 ሄክታር መሬት ከወዲሁ ተለይቶ የጉድጓድ መቆፈር ስራው እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን የሰከላ ወረዳ አርሶ አደር መኮነን ልንገር እንደገለጹት ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር መጀመሩ ተራቁተው የነበሩ አካባቢዎችን መልሰው በደን እንዲሸፈኑ ለማድረግ አስችሏል። መርሃ ግብሩ ለመኖ ፣ በንብ ማነብና እንስሳት እርባታ እያስገኝ ያለውን ተጠቃሚነት ለማስፋት በመጭው ክረምት በሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በግልና በወል ቦታዎች ችግኝ ለመትከል ጉድጓዶችን እያዘጋጀን ነው ብለዋል። የሚተከሉት ችግኞች አያስገኙ ያለውን ጠቀሜታ በመረዳት በየዓመቱ ችግኞችን እያለማሁ ነው ያሉት ደግሞ በደቡብ ጎንደር ዞን የደራ ወረዳ አርሶ አደር ካሴ መንግስት ናቸው። በመጭው ክረምት የሚተከሉ ችግኞች ተንከባክበን በማሳደግ ለውጤት ለማብቃት ከወዲሁ ዝግጅት ጀምረናል ነው ያሉት። ባለፈው ክረምት በነቃ የህዝብ ተሳትፎ ከተተከለው ከአንድ ነጥብ አራት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥ 80 በመቶ የሚሆነው መጽደቁን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በአፍሪካ የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ለመከላከል ሀገራት ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል
May 19, 2026 949
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በአፍሪካ የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ለመከላከል ሀገራት ቅንጅታዊ አሰራራቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ፀባይ ትንበያ ማዕከል ጋር በመተባበር ለሁለት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየውን 73ኛውን የምስራቅ አፍሪካ የአየር ፀባይ አዝማሚያ ትንተናና ትንበያ ፎረም ተጠናቋል። በፎረሙ የቀጣናው ሀገራት ተወካዮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አጋር ድርጅት ተወካዮች እና ሌሎች አካላት ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና በዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዚዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ባለፉት ሁለት ቀናት በአፍሪካ ቀንድ ዙርያ ያሉ የኢጋድ አባል ሀገራት ያለፈው የበልግና መጪው ክረምት ወቅት የሚጠበቀውን የአየር ጠባይ ትንበያን አስመልክቶ ተወያይተዋል። በዚህም ሁሉም ሀገራት ከራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ በመነሳት የራሳቸውን የሜቲዎሮሎጂ መረጃዎችንና ከአካባቢያቸው አየር ሁኔታ በማገናዘብ ትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቅያ የሚሰጡበት ሁኔታ ላይ መነጋገራቸው አንስተዋል። ከአየር ትንበያው በመነሳትም የሚኖረው የአየር ሁኔታ በግብርና፣በውሃ፣በጤና ላይ ሊያደርሰ የሚችለው አሉታዊና አዎንታዊ ተፅእኖ በመገምገም ለቀጣይ ዝግጅት የሚደረግበት መሆኑ ተናግረዋል። እንዲሁም በህይወትና በንብረት ላይ ሊደርስ የሚችለውን የአደጋ ተጋላጭነትን ከመቀነስ አንፃር ጉልህ ድርሻ ያለው በመሆኑ መሰል መድረክ መዘጋጀቱ ጠቀሜታው የላቀ ነው ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚያጋጥሙ አደጋዎች በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ አደጋ እያደረሰ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ይህን ለመከላከል ሀገራት በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና የመተግበሪያ ማዕከል(ICPAC) ዋና ዳይሬክተር አብዲ ፊዳር (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የኢጋድ አባላት ሀገራት መረጃን መሰረት ያደረገ መረጃ በመለዋወጥ በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳሰበዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 2288
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 1330
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 1253
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በአዲስ አበባ ይካሄዳል
May 13, 2026 1295
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በሕብረቱ ዋና መቀመጫ ዛሬ በአዲስ አበባ ይደረጋል። በውይይቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እንደሚገኙ ይጠበቃል። ውይይቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል በአፍሪካ ልማት እና በዓለም አቀፍ አስተዳደር ዙሪያ ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ቅንጅት፣ የጋራ ተጠያቂነት እና ትብብርን በልማት፣ በአስተዳደር፣ በሰብአዊ ድጋፍ እና በሰላም ግንባታ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ያላቸውን ትስስር ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ይካሄዳል። በዚህ የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ላይ በርካታ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች የሚዳሰሱ ሲሆን፣ በተለይም የአጀንዳ 2063 እና የሁለተኛው የአስር ዓመት ምዕራፍ የትግበራ ዕቅድ አፈፃፀምን ማፋጠን እንዲሁም አፍሪካን በዓለም አቀፍ ፖሊሲ እና አስተዳደር ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና መጠበቅ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል። በተጨማሪም "ከጥገኝነት ወደ ሉዓላዊነት" የተሸጋገረ የልማት ፋይናንስ፣ የ2026 የአፍሪካ ሕብረት የዓመቱ መሪ ቃል የሆነው ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና የንጽህና አጠባበቅ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ተቋማት ሪፎርም እና አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ያላትን ውክልና የተመለከቱ ጉዳዮች ውይይት ይደረግባቸዋል። መድረኩ ለአህጉራዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔዎችን ማምጣት፣ የአገር ውስጥ ሀብት ማሰባሰብን ማሳደግ፣ የወጣቶች እና የሴቶች ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዲሁም በአህጉራዊ እና በዓለም አቀፍ የልማት የቅድሚያ ትኩረቶች መካከል ያለውን ትስስር ማጠናከር ወሳኝ መሆኑ አጽንኦት የሚሰጥበት እንደሆነ ተመላክቷል። ከውይይቱ ከሚጠበቁ ውጤቶች መካከል የተሻለ ስትራቴጂካዊ ቅንጅት፣ ፍትሐዊ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ፣ በአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ቃል ዙሪያ ጠንካራ ቅንጅት መፍጠር እና በተባበሩት መንግሥታት ሥርዓት ውስጥ ፍትሐዊ የአፍሪካ ውክልና እንዲኖር የቀረቡ ጥሪዎችን ማጠናከር እንደሚገኙበት ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የውይይቱን ውጤቶች አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ይሰጣሉ።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 1595
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 1870
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 1692
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች
May 3, 2026 1754
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር እያሸጋገራት ይገኛል።የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የመሰረተ ልማት እና የተቋማት ግንባታ ስራዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋንኛ ስራዎች ናቸው። ለውጡን ተከትሎ መንግስት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን ስትራቴጂ በመቅረጽ የዲጂታላይዜሽን ስራውን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶ አድርጎታል። የለውጡ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ ቴክኖሎጂን እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመቁጠር "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን አጠቃላይ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ተግባር ገባ።ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱን የዲጂታል ጉዞ ከመሰረቱ የለወጠ ሲሆን፣የመጀመሪያው ትልቅ እርምጃም የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ነበር። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ የኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል።በተለይም የአምስተኛ ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን አስችሏታል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ለውጡ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ውጤት አምጥቷል።እንደ ቴሌብር (telebirr) ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ምንም የባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ፣ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር ትልቅ መደላድል ፈጥረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ አድማስ ይበልጥ አስፍተውታል። የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ራዕይ ለዓለም ያሳየችበት አጋጣሚ ነው።ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የካንሰር ህመምንና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ መለየት የሚያስችሉ የኤአይ ውጤቶችን አበልጽጓል። በግብርናውም ረገድ የአፈርን ለምነትና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ዋስትና ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል ዓለም ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የፋይዳ (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን መረጃ በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የለውጡ ፍሬያማነት ማሳያ ነው።የሳይንስ ሙዚየምም የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያሳይና የሀገሪቱን ቴክኖሎጂ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ሆኗል።የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቅርቡ መጠናቀቁ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2025 ስትራቴጂው መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዲጂታል 2030ን ይፋ ሲያደርጉ የነበረው ትልቁ መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች የሚል ነው። ስትራቴጂው በዋናነት"የፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት፣ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠር፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) አድርጎ መገንባትን እንደ ዋነኛ ግብ አስቀምጧል። ይህም ሁሉን አቀፍ የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ የመንግስት አገልግሎቶችን መቶ በመቶ ወረቀት አልባ በማድረግ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) በግብርና፣ በጤናና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ በስፋት በመተግበር የምርታማነት አብዮት መፍጠርን ያለመ ነው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ስራ በአህጉራዊ ደረጃ ያለውን ተቀባይነትና የተሰጣትን ትልቅ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት የቴክኖሎጂ ከፍታ፣ ሀገሪቱን በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ተፎካካሪ ብቻ ሳይሆን የፈጠራ ምንጭ እንድትሆንም እያደረጋት ይገኛል። በዚህ ረገድም የቀጣዩ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ስኬትም ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና በቴክኖሎጂ የበለጸገች ሀገር የማድረግ ራዕይን ለማሳካት እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ ያገለግላል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 250
ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት
May 17, 2026 3890
በኢዜአ ዐይን …! በዮሐንስ ደርበው እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉን የሚሉ እሮሮዎች በተለያዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሲነሱ ቆይተዋል። በተለይም በአንዳንድ ተቋማት መንግሥታዊ አገልግሎት ለማግኘት እዚያም እዚህም መንከራተት፤ደግሞም ወረፋ በመጠበቅ መጉላላት ብሎም ለጊዜና ገንዘብ ወጪ መዳረግ ይስተዋላል የሚሉ ሐሳቦች ተስተጋብተዋል። ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ባሳለፍነው ሳምንት … መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል አሠራር በመንደፍ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ አስጀመረ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማዕከሉ አገልግሎት ባስጀመሩበት ወቅትም ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው ብለው ነበር። አሁን ላይም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ነው።መስፋፋቱም በማዕከላት ብዛት፣በአገልግሎት መስጫ መስኮቶች ቁጥር እና በአገልግሎት ዐይነቶች እየተገለጠ ነው። በዚህም በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት የተደራጁ ሲሆን ይህ አሃዝም ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እና ያለውን ፈጣን እድገት ያመላክታል። ጉዳዩ የዜጎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ማላቅ፤ ብልሹ አሠራርንም መቅረፍ ነውና መንግሥት በልዩ ትኩረት ይዞታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ አሥተዳደርና በሐረሪ ክልል ጉብኝት ባደረጉበት ወቅትም፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የምልከታቸው አካል ማድረጋቸው ለጉዳዩ የተሰጠውን ከፍያለ ትኩረት ያሳያል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሶብ የሞባይል አገልግሎትን በመረቁበት ወቅት ደግሞ፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ብለዋል። አክለውም፤በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች ዕርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል፤ ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፤ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ መሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል ማለቱም ይታወቃል። የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ደግሞ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ ያስቻለ ስኬት ተገኝቷል ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ የመንግሥት አገልግሎቶችም ዜጋ ተኮር፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አብራርተዋል። በዲጂታል 2030 የአገልግሎት አሰጣጥ አመላካች ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚጠቀሱ 50 ሀገራት መካከል አንዷ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ዜጎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በኦንላይን በየትኛውም ቦታ ሁሉንም አገልግሎቶች እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ ስለመሆኑም እንዲሁ። አገልገሎቱን ያገኙ አስተያየት ሰጭዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ እንግልትን ያስቀረ፣ ጊዜና ወጭን የቀነሰ ነውና ይስፋፋ፤ ተጠናክሮም ይቀጥል። #መሶብ_የአንድ_ማዕከል_አገልግሎት #የዜጎችን_እንግልትና_ብልሹአሠራርን_መቅረፍ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #በኢዜአ_ዐይን
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 17, 2026 1970
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 2 እስከ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ጋር መምከራቸው ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም በኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል። ለነበረን ጠቃሚ የሐሳብ ልውውጥና ቀጣይነት ላለው አጋርነትም ምስጋናዬ የላቀ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ በኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና በፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በጋራ አዘጋጅነት በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካፍለዋል። በዚሁ ወቅትም በተለይም የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት እና የኃይል ሽግግርን በተመለከተው ውይይት ላይ ከተሞክሯችን የተቀዱ ከፍ ያሉ ሐሳቦች ተነስተዋል ብለዋል። አክለውም፤ ኢትዮጵያ በተነሱት ሁለት ዘርፎች የጀመረችውን ሥራ በማጠናከር የላቀ ሚና መጫወቷን ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንኳን ደህና መጡ ስል ሁልጊዜም በልዩ ኩራትና ደስታ ነው ሲሉ ተቀብለዋቸዋል። ከአቀባበሉ በኋላም፤ መሪዎች በጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በዚህም መሠረት፤ በታዳሽ፣ የተቀናጀ እና ዘላቂ ኃይል እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራምን ለመተግበር የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ ብድርን ጨምሮ የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የመንግሥትና የግል አጋርነት አዲስ የማዕቀፍ እና የፍኖተ ካርታ ስምምነት ተፈርሟል። · ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ማውጣቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርገዋል። እነዚህ አራት ቴምብሮች እ.ኤ.አ. በ1945 በሳን ፍራንሲስኮ የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን ከመፈረም ጀምሮ፤ በኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን እስከማሰማራት እና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ እስከ ማስተናገድ ያለውን የጋራ ታሪካችንን የሚተርኩ ናቸው ብለዋል። በዓለም የፖስታ ኅብረት በኩል ለ192 ሀገራት የተሰራጩት እነዚህ ቴምብሮች፤ ለአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን ለትውልድ ሁሉ የሚተርፍ የታሪክ ዐሻራ ማሳያ መሆናቸውንም አስታውቀዋል። በተያያያዘም፤ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ በዘመናዊው ታሪክ ውስጥ እጅግ ፈታኝ በሆነ ወቅት ላይ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር ጥልቅ አድናቆታችንን እንገልጻለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የተባበሩት መንግሥታት የጸናው ሀገራት ከመከፋፈል ይልቅ ውይይትን ስለመረጡ መሆኑን አስገንዝበው፤ ኢትዮጵያም ይህንኑ የሁልጊዜ ምርጫዋን ታጸናለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም የምክክር ባህል እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበው፤ ጠንካራ የሲቪክ ማኅበረሰብ ባህል ግንባታ ደግሞ ያላሰለሰ የመነጋገር ልምምድ እና የሰከነ የወል መደማመጥን ግድ ይላል ብለዋል። የእስካሁን ሂደቱም በማኅበረሰባችን በየደረጃው የመደማመጥን ከፍ ያለ ጠቀሜታ አሳይቷል ሲሉም ገልጸዋል። ሂደቱ በሀገራችን ሁሉም ማዕዘናት የሚገኙ ከ90 በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን አመለካከቶች እና የውይይት ውጤቶች ያንፀባረቀ ሆኗልም ነው ያሉት። ለሀገር ወሳኝ ፋይዳ የያዘው የምክክሩ ምዕራፍ ተጨባጭ ውጤት ወደሚያስገኘው ቀጣይ ምዕራፍ በሚሸጋገርበት በዚህ ወቅት፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለሀገራችን ሰላም፣ አንድነት እና ዘላቂ መረጋጋትን የሚያረጋግጥ የጋራ ፅኑ አቋም እና ገንቢ በሆነ መንገድ አስተዋፅኦ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል። · የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን በመረቁበት ወቅት፤ ፓርኩ አስተማማኝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጀመርነው የብልጽግና ጉዞ ተደማሪ እመርታ ነው ብለዋል። ለመካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች ምቹ የንግድ ከባቢ ከመፍጠር ባሻገር በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶቻችን የሥራ ዕድል ይከፍታል ሲሉም ገልፀዋል። ፓርኩ የሀገራችን አምራቾች አቅማቸውን በማጎልበት፣ ምርታማነታቸውን ማሳደግና ተወዳዳሪነታቸውን በመጨመር ለከተማችን፣ ለሀገራችንና ለቀጣናው የሚተርፉበት ታላቅ እድልን ይዟል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተኪ ምርቶችን በማምረት በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛና ቀልጣፋ የንግድ ትስስር ይፈጥራል፤ ምርቶችን ደግሞ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይጫወታል ሲሉ አስረድተዋል። · ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ መጀመር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔን ባስጀመሩበት ወቅት፤ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ቆራጥ ጥረት ውስጥ የሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል በማድረግ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በመላ ሀገሪቱ ከ35 ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት የነጻና አስገዳጅ ትምህርት ተደራሽ እንዲሆን እያደረግን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር ላይ መሥራት በመሆኑ ተባብረን፣ በጊዜ የለንም መንፈስና በትጋት እንሥራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። · የፖሊሲ ቀን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ ባሳላፍነው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው የፖሊሲ ቀን ተከብሯል። በዚሁ ወቅትም፤ ውጤታማ ፖሊሲ ለሀገራዊ ዕድገት የጀርባ አጥንት መሆኑን አስገንዝበው፤ መንግሥት በግልፅ፣ ተተግባሪና ጥራት ባላቸው ፖሊሲዎቹ ለሕዝብ የገባውን ቃል እየተገበረ ስኬትም እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ሀገራችን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ በጂኦ-ፖለቲካዊና በቴክኖሎጂ ለውጦች ላይ ቀድሞ ምላሽ የሚሰጡ ጥናቶች ያስፈልጋሉ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በዕውቀት ላይ ኢንቨስት በማድረግ እና ለማስረጃዎች ዋጋ በመስጠት፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ የፖሊሲ ሥነ-ምኅዳር ለመገንባት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ለዚህ ስኬት ሁላችንም በጋራ እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
የጤና ነገር
May 15, 2026 1792
በዮሐንስ ደርበው ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ሾተላይ የሚከሰተው RH-Negative የሆነች እናት RH-Positive የሆነ ፅንስ በምታረግዝበት ወቅት የእናትየው በሽታ የመከላከል ሥርዓት የፅንሱን ደም እንደ ባዕድ ነገር በመቁጠር በሚያመነጨው ንጥረ-ነገር (Antibodies) አማካኝነት መሆኑን የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። የጽንስና ማህጸን ስፔሻሊስት ዶክተር ዳንኤል ኃብተማርያም ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ከወሊድ ጋር በተያያዘው አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ወይም ሾተላይ እየተባለ በሚጠራው በጽንስ ላይ የሚያጋጥም ችግር ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሾተላይ ወይም አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ዳንኤል ማብራሪያ፤ ሰዎች ከሚታወቁበት አራቱ የደም ዓይነቶች ምደባ (ኤ፣ ቢ፣ ኤቢ እና ኦ) በተጨማሪ በቀይ ደም ኅዋስ ሰርፌስ ላይ በፕሮቲን መኖርና አለመኖር ይለያሉ። በዚህም መሠረት አር ኤች ፖዘቲቭ (RH+) እና አር ኤች ኔጌቲቭ (RH-) ተብለው እንደሚከፈሉ ያስረዳሉ። በዚህ ምደባ መሠረት ከአጠቃላይ ሕዝቡ 85 በመቶው አር ኤች ፋክተር ፖዘቲቭ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ማለት በቀይ ደም ኅዋሳቸው ሰርፌስ ላይ ፕሮቲን አላቸው ማለት ነው ይላሉ። 15 በመቶው ደግሞ አር ኤች ኔጌቲቭ ወይም በቀይ የደም ኅዋሳቸው ሰርፌስ ላይ ፕሮቲን የሌላቸው ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። አክለውም አር ኤች ኔጌቲቭ ወይም ፖዘቲቭ መሆን በሽታ እንዳልሆነ በአጽንኦት ገልጸው፤ ከወላጆች የሚወረስ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ አንድ ልጅ ሲወለድ እንደ ወላጆቹ አር ኤች ፋክተር መሠረት አር ኤች ፖዘቲቭ ወይም አር ኤች ኔጌቲቭ ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። ይህን በምሳሌ ሲያስረዱም፤ አንዲት ሴት አር ኤች ፋክተሯ ኔጌቲቭ ሆኖ ጽንሷ ደግሞ አር ኤች ፖዘቲቭ ቢሆን ተገቢው የሕክምና ክትትል ካልተደረገ ብሎም የእናትና ልጅ ደም ንክኪ ከተፈጠረ የበሽታ መከላከል ሥርዓቷ የሚያመነጨው አንቲ ቦዲ ጽንሱን እንደ ባዕድ ነገር ስለሚቆጥረው ጉዳት (ሾተላይ) ያስከትላል ይላሉ። የአንቲ ቦዲ ሥራ ሴቷ ለአር ኤች ፖዘቲቭ የምትጋለጥበት ሁኔታ ከተፈጠረ ጽንሱን (አር ኤች ፋክተሩ ከእሷ ተቃራኒ ሲሆን) እንደ ባዕድ ነገር ቆጥሮ ሴትዮዋን ለመከላከል በጽንሱ ላይ ጥቃት ማድረስ መሆኑንም አመላክተዋል። መፍትሔው ምንድን ነው? ለማንኛውም ጤናማ የእርግዝና ሂደት የሕክምና ክትትል ማድረግ ቀዳሚ መፍትሔ መሆኑን መክረዋል። ከሾተላይ ጋር በተያያዘ ደግሞ በእርግዝና ወቅት የሚስትና ባልን አር ኤች ፋክተር መለየት ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህን ተከትሎም አር ኤች ፋክተራቸው ተመሳሳይ ከሆነ ጽንሱም ከእነሱ ጋር ስለሚመሳሰል ጤናማ እንደሚሆን ገልጸዋል። በአንጻሩ ግን፤ አር ኤች ፋክተሯ ኔጌቲቭ የሆነች ሴት የባለቤቷ አር ኤች ፋክተር ፖዘቲቭ ከሆነ ወይም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ ሰውነቷ መከላከያ አምርቷል ወይስ አላመረተም የሚለው በሕክምና ምርመራ እንደሚታወቅ አስረድተዋል። ይህ ምርመራ ሲሠራ ውጤቱ ኔጌቲቭ ከሆነ ወይም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ ሰውነቷ መከላከያ አላመረተም የሚል ከሆነ በዚህኛው እርግዝናም ለአር ኤች ፖዘቲቭ ተጋልጣ፣ የእናትና የጽንስ ደም ንክኪ ኖሮ መከላከያ እንዳታመርት የሚሰጥ ሕክምና እንዳለ አረጋግጠዋል። ይህ ሕክምናም 28ኛ ሳምንት ላይ በመርፌ ለመጀመሪያ ጊዜ ይሰጣል ብለዋል። ከወለደች በኋላ ደግሞ የተወለደው ልጅ አር ኤች ፋክተር ታይቶ እንደእናቱ ከሆነ ተጨማሪ መድኃኒት እንደማያስፈልግና ከአባቱ ጋር ከተመሳሰለ ግን (አር ኤች ፖዘቲቭ ከሆነ) በመርፌ ተጨማሪ መድኃኒት በወለደች በ72 ሠዓት ውስጥ በመስጠት ለቀጣይ እርግዝናዎች ሰውነቷ መከላከያ እንዳያመነጭ ማድረግ እንደሚቻል አብራርተዋል። በሌላ በኩል ከሾተላይ ጋር በተያያዘ የሚደረጉ ሳይንሳዊ ያልሆኑ ልማዳዊ ድርጊቶችን ኮንነው፤ ትክክለኛው መፍትሔ ያለው የሕክምና ክትትል በማድረግ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲሁም፤ በተለይም የጎንዮሽ ህመም ያለባቸው ሴቶች (የኩላሊት፣ የደም ግፊት፣ ስኳር እና ሌሎችም) ቀድመው ሐኪም አማክረው ወደ እርግዝና ቢገቡ እንደሚመከር ገልጸው፤ የቅድመ እርግዝና ክትትል ማድረግ ካልተቻለ እንኳን በእርግዝና ወቅት በአግባቡ ክትትል ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል። ለመከላከያ ትልቅ ትኩረት መስጠት ችግሩ ተፈጥሮ ከመታከም የተሻለና ተመራጭ መፍትሔ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። #የጤና_ነገር #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 7136
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 4320
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 10108
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 8587
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 1831
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 2409
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።