ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ሜሲ የዓለም ዋንጫን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረ ወሰን በሰበረበት ጨዋታ አርጀንቲና ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች
Jun 22, 2026 445
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የምድብ 10 መርሐ ግብር አርጀንቲና ኦስትሪያን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በዳላስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሊዮኔል ሜሲ በ38ኛው እና በ95ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥሯል። ሜሲ በዓለም ዋንጫው ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 18 በማድረስ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን ክብረ ወሰን ከጀርመኑ ሚሮስላቭ ክሎዝ (16 ጎል) ተረክቧል። ሜሲ በስምንተኛው ደቂቃ ቡድኑ ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ስቷል። የ38 ዓመቱ ተጫዋች በአጠቃላይ ለሀገሩ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 122 በማድረስ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን አጠናክሯል። ውጤቱን ተከትሎ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ አርጀንቲና በስድስት ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፍ ገብታለች። ኦስትሪያ በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዚሁ ምድብ ጆርዳን ከአልጄሪያ በሳንፍራንሲስኮ ቤይ ኤሪያ ስታዲየም ከማለዳው 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሁለቱ ሀገራት በመጀመሪያ ጨዋታቸው ሽንፈት አስተናግደዋል።
የኢትዮጵያን የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብቶች ምርታማነት የማሳደግ የዝርያ ማሻሻል ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
Jun 22, 2026 510
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ):- የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ዝርያን የሚያሻሽሉ ሙያተኞችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል። በዚህም ኢንስቲትዩቱ ከሰኔ 08 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በሰው ሰራሽ ማዳቀል የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ዝርያን ለማሻሻል ለሙያተኞች የሰጠውን ስልጠና በማጠናቀቅ ሰልጣኞችን አስመርቋል። የግብርና ሚንስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ፤ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ያላት ሀገር ናት ብለዋል። የኢትዮጵያን የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ለማሻሻልም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችንና የአሰራር ሥርዓቶችን በመቅረፅ እየተሰራባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ለማሻሻል እየተሰራበት የሚገኘው የሰው ሰራሽ ማዳቀል ሥነ-ዘዴ ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩትም የሰው ሰራሽ ማዳቀል ሙያተኞችን በብዛትና በጥራት ለማፍራት መሰረት መጣሉን አንስተዋል። በኢንስቲትዩቱ ትምህርትና ስልጠና የተሰጣቸው ሙያተኞችም የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን በማሻሻል ህዝባቸውን ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የመደመር መንግሥት የገጠር ሽግግርን ለማሳለጥ ለእንስሳት ሃብት ምርታማነት ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸዋል። በዚህም የመንግሥትን መርህ ታሳቢ በማድረግ በሰው ሰራሽ የማዳቀል ሥነ-ዘዴ የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትና ጤንነት ሙያተኞችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ለምርቃት ለበቁት ሰልጣኝ ሙያተኞችም በእንስሳት እንክብካቤና አመጋገብ፣ በሽታ መከላከልና ጤና አጠባበቅ፣ ምርት ማቀነባበሪያና የገበያ ትስስር ትምህርት መሰጠቱን አስረድተዋል። በስልጠናውም የያቤሎ፣ ጂንካ፣ ባኮ፣ አዳሚቱሉ፣ የዓርባ ምንጭ ምርምር ማዕከላት፣ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት እንዲሁም የግል እርሻ ሙያተኞች መሳተፋቸውን አስረድተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ባለስልጣኑ የትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነቱን ማስፋፋትና አቅሙን ማጠናከር አለበት
Jun 22, 2026 425
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነቱን ማስፋፋትና አቅሙን ማጠናከር እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት የአስራ አንድ ወራት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል። የቋሚ ኮሚቴው አባላት ባለስልጣኑ ዓለም አቀፍ እውቅናን ለማግኘት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትና ሌሎች ሥራዎች በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ጠይቀዋል፡፡ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አሕመድ አብተው (ዶ/ር) ባለፉት ዓመታት የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በተከናወኑ ተግባራት የትምህርት ተቋማት ጥራት ላይ ሰፊ ለውጥ መመዝገቡን አመላክተዋል፡፡ የአካዳሚክ ጥራት ኦዲት፣ የክትትልና ቁጥጥር፣ የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ፣ የአቻ ግመታ መመሪያዎችና ስታንዳርዶች ሥራ ላይ በመዋላቸው የባለስልጣኑ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እያደገ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዘገባ ስርዓት ውስጥ እንዲገቡ መደረጉንም አክለዋል። የትምህርት ዘርፍ ፍቃድ እና የፍቃድ ዕድሳት እንዲደረግላቸው ለጠየቁ ለዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች ተገቢውን የጥራት መመዘኛ በማድረግ ፍቃድ መሰጠቱንም ገልጸዋል። የአጠቃላይ የትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነት ለማስፋፋትም የክልሎችን አቅም የማጎልበት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ባለስልጣኑ ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎች እውቅና ለማግኘት የሰነድና ሌሎች ዝግጅቶች እየያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፣ በባለስልጣኑ የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል፡፡ ሪፎርሙ በትምህርት ጥራነትና አግባብነትን ላይ ተጨባጭ ውጤት ማመጣቱንና የትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነት እንዲሰፋ ማስቻሉን ነው ያነሱት። በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የተገልጋዮች እርካታ፣ የአካዳሚክ ጥራት ኦዲት እና በትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነት ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ባለስልጣኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኝ በማድረግ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ ፕሮግራሞች በሀገርና በዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኙ ማድረግና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራትን መደገፍ ይገባል ብለዋል። ቋሚ ኮሚቴው አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡      
ሀዲያ ሆሳዕና ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
Jun 22, 2026 330
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሀዲያ ሆሳዕና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብሩክ በየነ በመጀመሪያ አጋማሽ ማብቂያ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሀዲያ ሆሳዕና በ46 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 13ኛ ከፍ ብሏል። በሊጉም 11ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 12ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ42 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ባለፉት አራት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ዛሬ አስቀድመው በተደረጉ የ36ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ፋሲል ከነማ አርባምንጭ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ አርባምንጭ ከተማ ከሊጉ የወረደ የመጀመሪያ ቡድን ሆኗል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 ረቷል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የ36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተጠናቋል።
ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቀነስ የሚያስችሉ የጋራ ተጨባጭ መፍትሔዎችን መተግበር ይገባል
Jun 22, 2026 509
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቀነስ የሚያስችሉ የጋራ ተጨባጭ መፍትሔዎችን መተግበር እንደሚገባ የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዝደንት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንት ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል። የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዝደንት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በሳምንቱ እየተሳተፉ ነው። በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በሰኔ ወር በለንደን ታይቶ የማይታወቅ የሙቀት መጠን ሊኖር እንደሚችል መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ጠቅሰዋል። ይህም የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መከላከል እንደሚያስፈልግ ሁነኛ ትምህርት የሚያስተላልፍ መሆኑን ገልጸዋል። እየተስተዋለ ያለው ከፍተኛ የሙቀት መጠን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጨባጭ የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት መርሃ ግብር ቀርጾ መተገበር የግድ መሆኑን ያስገነዘበ ነው ብለዋል። በለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንትም ለዓለም የሚበጁ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ መፍትሔዎችን ማፍለቅ ከሁሉም የሚጠበቅ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። የለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንት እስከ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።  
የሚታይ
የኢትዮጵያን የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብቶች ምርታማነት የማሳደግ የዝርያ ማሻሻል ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
Jun 22, 2026 510
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ):- የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ዝርያን የሚያሻሽሉ ሙያተኞችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል። በዚህም ኢንስቲትዩቱ ከሰኔ 08 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በሰው ሰራሽ ማዳቀል የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ዝርያን ለማሻሻል ለሙያተኞች የሰጠውን ስልጠና በማጠናቀቅ ሰልጣኞችን አስመርቋል። የግብርና ሚንስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ፤ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ያላት ሀገር ናት ብለዋል። የኢትዮጵያን የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ለማሻሻልም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችንና የአሰራር ሥርዓቶችን በመቅረፅ እየተሰራባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ለማሻሻል እየተሰራበት የሚገኘው የሰው ሰራሽ ማዳቀል ሥነ-ዘዴ ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩትም የሰው ሰራሽ ማዳቀል ሙያተኞችን በብዛትና በጥራት ለማፍራት መሰረት መጣሉን አንስተዋል። በኢንስቲትዩቱ ትምህርትና ስልጠና የተሰጣቸው ሙያተኞችም የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን በማሻሻል ህዝባቸውን ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የመደመር መንግሥት የገጠር ሽግግርን ለማሳለጥ ለእንስሳት ሃብት ምርታማነት ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸዋል። በዚህም የመንግሥትን መርህ ታሳቢ በማድረግ በሰው ሰራሽ የማዳቀል ሥነ-ዘዴ የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትና ጤንነት ሙያተኞችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ለምርቃት ለበቁት ሰልጣኝ ሙያተኞችም በእንስሳት እንክብካቤና አመጋገብ፣ በሽታ መከላከልና ጤና አጠባበቅ፣ ምርት ማቀነባበሪያና የገበያ ትስስር ትምህርት መሰጠቱን አስረድተዋል። በስልጠናውም የያቤሎ፣ ጂንካ፣ ባኮ፣ አዳሚቱሉ፣ የዓርባ ምንጭ ምርምር ማዕከላት፣ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት እንዲሁም የግል እርሻ ሙያተኞች መሳተፋቸውን አስረድተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቀነስ የሚያስችሉ የጋራ ተጨባጭ መፍትሔዎችን መተግበር ይገባል
Jun 22, 2026 509
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቀነስ የሚያስችሉ የጋራ ተጨባጭ መፍትሔዎችን መተግበር እንደሚገባ የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዝደንት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንት ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል። የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዝደንት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በሳምንቱ እየተሳተፉ ነው። በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በሰኔ ወር በለንደን ታይቶ የማይታወቅ የሙቀት መጠን ሊኖር እንደሚችል መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ጠቅሰዋል። ይህም የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መከላከል እንደሚያስፈልግ ሁነኛ ትምህርት የሚያስተላልፍ መሆኑን ገልጸዋል። እየተስተዋለ ያለው ከፍተኛ የሙቀት መጠን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጨባጭ የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት መርሃ ግብር ቀርጾ መተገበር የግድ መሆኑን ያስገነዘበ ነው ብለዋል። በለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንትም ለዓለም የሚበጁ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ መፍትሔዎችን ማፍለቅ ከሁሉም የሚጠበቅ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። የለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንት እስከ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።  
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የዘላቂ ልማት ግቦች በተግባር እየተተረጎሙ መሆናቸውን የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው
Jun 22, 2026 417
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የዘላቂ ልማት ግቦች በተግባር እየተተረጎሙ መሆናቸውን የሚያሳይ ህያው ምስክር መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና የተቋማት ክትትል ሚኒስትር ዲኤታ አክሊሉ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አመራርና ሠራተኞች ጋር በመሆን በየካ ተራራ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል።   በዚሁ ወቅት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና የተቋማት ክትትል ሚኒስትር ዲኤታ አክሊሉ ታደሰ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የዘላቂ ልማት ግቦች በተግባር እየተተረጎሙ መሆናቸውን የሚያሳይ ህያው ምስክርና ቁልፍ ማሳያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ሰፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸው፤ በተደረገው አገራዊ ርብርብ 48 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውንና ዘንድሮም 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ መያዙን አስታውቀዋል። ዓለም በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በርካታ ጉዳቶችን እያስተናገደች ባለችበት በአሁኑ ወቅት፣ ዘላቂ ዕድገትን ማረጋገጥ የሚቻለው ተፈጥሮን በመጠበቅና በመንከባከብ መሆኑን ጠቁመዋል።   ኢትዮጵያ እያከናወነችው ባለው በዚህ መርሃ ግብር በረሃማነትና የአየር ንብረት መዛባት በጉልህ እየቀነሰ መምጣቱንም ተናግረዋል። የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል አካሉ ካሳ በበኩላቸው በዚሁ ስፍራ ችግኞችን መትከላቸውን ገልጸው፤ አካባቢው ቀድሞ ከነበረበት መራቆት በጉልህ መለወጡን መስክረዋል። የአረንጓዴ አሻራ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መርሃ ግብር መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰራዊቱ ሀገር ከመጠበቅ ጎን ለጎን በዚህ አገራዊ ጥሪ ላይ አሻራውን እያሳረፈ እንደሚገኝና መርሃ ግብሩም ሰራዊቱ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠብቀው መሆኑን አስገንዝበዋል። ከቤተ መንግሥት አስተዳደር የመጣው ሀብታሙ ዮናስ በበኩሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአመት ዓመት በተሳትፎም ሆነ በሚተከሉ ችግኞች ቁጥር እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ ዘንድሮ የተያዘው አገራዊ ዕቅድ ግቡን እንዲመታ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጠይቋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፈችው ምናለሸዋ ማንደፍሮም የአረንጓዴ አሻራ ለትውልድ የተሻለች ሀገር የምናስተላልፍበት በመሆኑ ሁላችንም አሻራችንን ማኖር አለብን ብላለች፡፡ በተመሳሳይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፈው ተመስገን በለጠ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ትልልቅ ውጤቶችን እያስገኘ መሆኑን ገልጾ የነገዋን ኢትዮጵያ የተሻለች ለማድረግ ሁሉም በጉልህ መሳተፍ እንዳለበት አሳስቧል።
የመስኖ ፕሮጀክቶችን በጥራትና ፍጥነት በማጠናቀቅ የልማት አቅም ለማድረግ የስታንዳርድ አሰራሮች ስራ ላይ ውለዋል
Jun 22, 2026 496
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በጥራትና ፍጥነት በማጠናቀቅ የልማት አቅም ለማድረግ የሚያስችሉ የስታንዳርድ አሰራሮች ስራ ላይ ማዋሉን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱረህማን አብደላ ገለፁ። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከክልል መስኖ ቢሮ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በውስጥ ስታንዳርድ ዝግጅትና ትግበራ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሂዷል።   የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱረህማን አብደላ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፣ አዲሱ ስታንዳርድ እያንዳንዳቸው የመስኖ ፕሮጀክቶች የሚያልፉበትን ሂደት በግልጽ ያስቀምጣል። ስታንዳርዱ በፌደራል ደረጃ ብቻ ሳይሆን በክልሎችም በሚገነቡ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ጭምር ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል። በትግበራው አማካኝነት ትልቁ የመስኖ ፕሮጀክቶች ፈተና የሆነው የዲዛይንና ጥናት ችግር ከስር መሰረቱ እንደሚፈታ ጠቁመዋል።   የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የመስኖ ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን መሪ ሰራ አስፈፃሚ ያሬድ ሙላት፣ ሰነዱን ሙሉ በሙሉ በውስጥ አቅም የተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ስታንዳርዱ ከህዳር 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ወደ ትግበራ መግባቱን አስታውቀዋል። በዚህም በመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ከዚህ ቀደም ይነሱ የነበሩ የጥራትና የዲዛይን ለውጥ ጥያቄዎች መስተካከሉን እና በርካታ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውን ጠቅሰዋል፡፡   በመድረኩ አስተያየት የሰጡት የሲዳማ ክልል የመስኖ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መስፍን በላይ ከዚህ ቀደም ጥናቶች በሚገባ ሳይጠናቀቁ ወደ ግንባታ በመገባቱ ፕሮጀክቶች ይጓተቱ እንደነበር አስታውሰዋል። የስታንዳርድ መዘጋጀት የትኛው ተግባር መቅደም እንዳለበት በግልጽ ስለሚያስቀምጥ ይህንን ክፍተት ሙሉ በሙሉ እንደቀረፈው ገልጸዋል።   የኦሮሚያ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር አለሙ ረጋሳ በበኩላቸው አሰራሩ ሀገር በዘርፉ የያዘችውን ትልቅ የመስኖ ልማት እቅድ በጥሩ ሁኔታ ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።   የአፋር ክልል መስኖና ቆላማ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኢንጂነር መሐመድ ሁማድ አሁን ላይ ስታንዳርዱ በመዘጋጀቱና ስራዎች በህግና በስርዓት መመራት በመጀመራቸው፣ ቀደም ሲል በዘርፉ ይታይ የነበረውን ተግዳሮቶችን መድፈኑን ተናግረዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ ለኢትዮጵያ ታላቅ ክብር እና ተሰሚነት አጎናጽፏታል- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 22, 2026 489
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ አረንጓዴ ዐሻራ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ረገድ ለኢትዮጵያ ታላቅ ክብር እና ተሰሚነት ማጎናጸፉን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ አረንጓዴ ዐሻራ በተባበሩ ክንዶችና በመደመር የከበረ እሳቤ የመስራት ምስክር ነው ብለዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሠራተኞች ጋር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጫካ ፕሮጀክት ዛሬ መካሄዱንም ጠቁመዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ እንደ ሀገር የውበት ምንጭ የኢኮኖሚ ተደማሪ አቅም ይሆናል ተብሎ ታቅዶ የተሠራና በውጤት ፍሬ አፍርቶ እየታየ ያለ ተግባር መሆኑን አመልክተዋል።   ይህ በተግባር የተደገፈ ግዙፍ የአረንጓዴ ልማት ጉዞ፣ ከኢኮኖሚያዊና የአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው አልፎ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ረገድ ለሀገሪቷ ታላቅ ክብር እና ተሰሚነት አጎናጽፏታል ነው ያሉት። የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ በመሳብ ላይ የሚገኘው ይህ ስኬት፣ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) በኩራት ለምታስተናግደው ታሪካዊ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ጠንካራና አስተማማኝ መሰረት መጣሉን ተናግረዋል።   ይህ ሁለንተናዊ እመርታ የመንግሥትንና የዜጎችን ትጋት የሚያሳይ፣ መላው ኢትዮጵያውያንን እጅግ ሊያኮራ የሚገባ ታላቅ ሀገራዊ ድል ነው ብለዋል። በዚህ ዓመት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ያቀድነውን ግብ ለማሳካት በኅብረት እንትከል፣ እንንከባከብ ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ
Jun 22, 2026 820
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ (ዶ/ር)ን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ውይይቱን አስመልክቶ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡   ውይይቱ ኢትዮጵያ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ስደተኞችን በማስተናገድ ረገድ ለምትጫወተው ወሳኝ ሚና ድርጅታቸው ያለውን አድናቆትና እውቅና ለመግለጽ ትልቅ አጋጣሚ መፍጠሩን ገልጸዋል። በተለይም ሀገሪቱ ስደተኞችን በብሔራዊ ሥርዓቱ ውስጥ ለማካተትና በሰብአዊ እርዳታ ላይ ብቻ ጥገኞች እንዳይሆኑ ለመርዳት በቅርቡ ይፋ ያደረገችውን የማካተት ፍኖተ ካርታን በአብነት ጠቅሰዋል። በፍኖተ ካርታው የትግበራ ሂደት ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም የጋራ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል፣ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ ኢትዮጵያ በቅርቡ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት በማጠናቀቋ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው፤ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክትም አስተላልፈዋል።
የብልፅግና ፓርቲ የሀገሪቱን ልማት ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ የጋራ ምክር ቤቱ አብሮ ለመሥራት ዝግጁ ነው
Jun 22, 2026 672
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የምርጫ አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ የከተማዋንና የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ፣ የጋራ ምክር ቤቱ በነቃ ተሳትፎ፣ በገንቢ ሂስና በአማራጭ ሃሳቦች አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቅን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። የጋራ ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተጠናቆ የብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ በማግኘት ማሸነፉን አስታውቋል። ምክር ቤቱ ይህ ምርጫ የከተማዋንና የሀገሪቱን የፖለቲካ ብስለት እንዲሁም የሕዝብን የሉዓላዊነት ስልጣን ያረጋገጠ ታሪካዊ መድረክ መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን ገልጾ፣ በሕዝብ ነፃ ውሳኔ አሸናፊ ለሆነው ለብልፅግና ፓርቲ እና በውድድሩ ተሳትፈው የምክር ቤት ወንበር ላገኙ ፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ምክር ቤቱ ስም ልባዊ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ታሪካዊው ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅና የዲሞክራሲ ባህል እንዲጎለብት በውድድሩ የተሳተፉ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ላበረከቱት አዎንታዊና ታሪካዊ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ የላቀ ምስጋና አቅርቧል። በምክር ቤቱ ስር የሚንቀሳቀሱም ሆኑ በምርጫው የተሳተፉ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሂደቱ ላሳዩት ከፍተኛ የፖለቲካ ጨዋነት፣ለሰላማዊ የሃሳብ ፉክክርና ለሕግ የበላይነት መገዛት የሚደነቅ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው፣ይህ የሰለጠነ አካሄድ ለዜጎች ሰፊ የአማራጭ አድማስ ከመፍጠሩም በላይ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ቁልፍ ሚና መጫወቱን አስገንዝቧል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በነፃነትና በሰላማዊ መንገድ ወጥተው የሰጡትን ድምፅና ያሳዩትን ምርጫ በሙሉ ልብ በመቀበል፣ ለሕዝብ ድምፅ ያለውን ፍጹም ክብርና እውቅና አረጋግጧል። የምርጫው ምዕራፍ በተሳካ ሁኔታ ቢጠናቀቅም፣የሀገር ግንባታ እና የሕዝብ አገልግሎት ቀጣይነት ያለው የጋራ ሃላፊነት በመሆኑ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ምክር ቤቱ አሳስቧል። አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ የከተማዋንና የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ፣ የጋራ ምክር ቤቱ በነቃ ተሳትፎ፣ በገንቢ ሂስና በአማራጭ ሃሳቦች አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ምክር ቤቱ በውድድሩ ተሳትፈው የምክር ቤት ወንበር ላገኙ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች፣ እንዲሁም በድጋሚ ለብልፅግና ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች እንኳን ደስ ያላችሁ ብሏል። መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ባለድርሻ አካላት ለሰላማዊው የምርጫ ሂደት ስኬት ላደረጉት ታሪካዊ አስተዋጽኦም ምስጋናውን አቅርቧል።
የኢትዮጵያ እና የዩናይትድ ኪንግደም ግንኙነት ይበልጥ ሊጠናከር ይገባል-ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Jun 22, 2026 611
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የኢትዮጵያና የዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል። በለንደን ከተማ የሲዳራ ግሩፕ (Sidara Group) ያዘጋጀው እንዲሁም በሌበር አፍሪካ ኔትወርክ (Labour African Network) እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም ኤምባሲ በጋራ በተሰናዳው የዲፕሎማቲክ እራት መርሐ ግብር ተካሄዷል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም የዕድገትና ብልጽግና አዳዲስ ዕድሎችን ለመጠቀም የውይይት እና የትብብር መድረኮች ወሳኝ ሚና አላቸው። የኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም ግንኙነት በመንግሥት ተቋማት መካከል ብቻ የተገደበ እንዳልሆነ ገልጸዋል። ትብብሩ በንግድ ድርጅቶች፣ በትምህርት ተቋማት፣ በዲያስፖራ ማህበረሰቦች እና በሁለቱ ሀገራት ዜጎች መካከል ባለው ዘላቂ ትስስር ላይ የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትም ለጠንካራ እና ዘላቂ አጋርነት ዋነኛው ምሰሶ ነው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ወቅታዊ የሪፎርም አጀንዳ እና የረጅም ጊዜ የልማት ትልሞችን አንስተዋል። በተለይም ኢኮኖሚውን ለማጠናከር፣ ለወጣቱ ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንዲሁም አካታች እና ዘላቂ ዕድገትን ለማስፈን እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን አንስተዋል።   የኢትዮጵያን ሕዝብ የአይበገሬነት አቅምና በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለውን አዲስ የተስፋ መንፈስ በመጥቀስም የወደፊቱ ጊዜ ብሩህ እንደሚሆን ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል በንግድ፣በኢንቨስትመንት፣በትምህርት፣ በምርምር፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራ (ኢኖቬሽን) እና በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም አቅም ዙሪያ ሰፊ የትብብር ዕድሎች መኖራቸውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰበ የመጣውን ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ በአግባቡ ለመወጣት እና ለሁለቱም ሀገራት ዜጎች ተጨባጭ ጥቅሞችን ለማስገኘት ጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት መፍጠር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም አሳስበዋል።   የሌበር አፍሪካ ኔትወርክ (LAN) ሊቀመንበር ኤርነስት አምቤ በንግግራቸው ኔትወርኩ፤ የአፍሪካ ድምጽ በዩናይትድ ኪንግደም የፖሊሲ ቀረጻ፣ የንግድ እና የዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ ጎልቶ እንዲሰማ በማድረግ ረገድ የተጫወተውን ጉልህ ሚና አድንቀዋል። አያይዘውም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከአፍሪካ ትላልቅ እና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ገበያዎች አንዱ መሆኑን በልዩ ሁኔታ አንስተዋል። በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን በበኩላቸው፥ የዲፕሎማሲ ሁነቱ እየተጠናከረ የመጣው የሀገራቱ የንግድ፣የኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ትብብር ለማስፋት መልካም አጋጣሚን መፍጠሩን ገልጸዋል።   ዩናይትድ ኪንግደም ከኢትዮጵያ እና ከአጠቃላይ አፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ አጋርነት ማደግ አዳዲስ ዕድሎችን፣ የጋራ ብልጽግናን እና አካታች ዘላቂ ዕድገትን ለማምጣት እንደሚያስችል መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ብልፅግና ፓርቲ በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Jun 22, 2026 544
ጅማ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ይፋ ባደረገው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት፣ ብልፅግና ፓርቲ በአብላጫ የምርክ ቤት መቀመጫ ማግኘቱ ይታወቃል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ታመነ ኃይሉ፤ ፓርቲው የጀመራቸውን ትልልቅ ፕሮጀክቶችና በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ፓርቲው ከዚህ ቀደም ያከናወናቸው ሰው-ተኮር ልማቶች አገሪቱን ከድህነት ለማውጣት ከፍተኛ አቅም ማበርከታቸውን የጠቀሱት አቶ ታመነ፤ በቀጣይም ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ርብርብ ሕዝቡና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ ይሰራሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሙደሲር መሐመድ በበኩላቸው፤ ፓርቲው ያቀዳቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ለሕዝብ ተጠቃሚነት ለማዋል ከታችኛው መዋቅር ጀምሮ ሙስናን የመታገል ተግባሩን ማጠናከር እንዳለበት ጠቁመዋል። ለዚህም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አሰራር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት፣ የሙስና መከላከያ ስልቶችን ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል። የአገርን ሰላም ማስከበርና ልማትን ማፅናት ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም ያሉት አቶ ሙደሲር፤ ጉዳዩ የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ እሳቸውም የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ሕዝቡ በምርጫ ሥልጣን የሰጠው ፓርቲ የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠርና ሕገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል የሚያደርገውን ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ደግሞ አቶ መልካሙ ቡላ እና አቶ በፀጋው አበራ ናቸው። አስተያየት ሰጪዎቹ የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ማንኛውንም ጥረት በንቃት በመደገፍ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አስታውቀዋል።
ምርጫው ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው-አብን
Jun 22, 2026 558
አዲስ አበባ፤ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፡-7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው ሲል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ገለጸ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ትናንት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫውን ሂደት ስኬታማነት በመግለጽ፤ ውጤቱን በጸጋ መቀበላቸውን እና በአብላጫ ድምጽ ላሸነፈው ብልጽግና ፓርቲም የመልካም ምኞት መግለጫ እያስተላለፉ ነው። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በበኩሉ ባወጣው መግለጫም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው ብሏል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ ወደ ተሻለ የፖለቲካ እና የማኅበረ-ኢኮኖሚ ምዕራፍ ለመሻገር ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ውሳኔ መሆኑንም አመላክቷል። የተመዘገበው ስኬት የማህበረሰባችን የአርቆ አሳቢነት ትሩፋት በመሆኑ ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባም ነው ብሏል በመግለጫው፡፡ ምርጫው ሕዝባችን ፈተናዎችን ተቋቁሞ በታሪክ የሚዘከር የአይበገሬነት ታሪክ የጻፈበት፣ ለዘላቂ ሰላምና እድገት የሚበጅ የፖለቲካ ባህል አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ ያደረገበት፣ በዋናነት የማኅበረ-ፖለቲካ ግብረ-ገብ እሴቶች ተቃራኒ የሆኑ ጯሂና እኩይ ድምጸቶችን ማሸነፍ የቻለበት፣ ለሰላም ሲባል ዋጋ የመክፈል ቁርጠኝነት የታየበትና ዋጋ የተከፈለበት መሆኑንም ነው የገለጸው። ሕዝብን ማሸነፍ አይቻልምና ድሉ የሰላም ወዳዱ ሕዝብ ሆኗልም ነው ያለው። ምርጫው ለውጫዊ የኢትዮጵያ ጠላቶችም ተስፋ ያስቆረጠ ክስተት መሆኑንም አብን ገልጿል። ዳያስፖራው ልማቶችንና የሰላም እንቅስቃሴዎችን እንዲደግፍ እንዲሁም ለሀገራዊ መረጋጋት ፋይዳ ከሌላቸው አጀንዳዎች ራሱን እንዲያርቅ አብን ጥሪ አቅርቧል። በመጨረሻም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምጽ ላገኘው ብልጽግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልካም ምኞቱን ገልጾ፤መጭው ጊዜ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ሁለንተናዊ ምዕራፍ የምናሻግርበት ነው ሲል ገልጿል።
የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሌሎች የምክክር ሂደቶች በምን ይለያል?
Jun 22, 2026 652
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክሩን ለማስተባበር ሥራውን ሲጀምር በስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ካስቀመጣቸው ምሰሶዎች አንዱና ዋነኛው አጀንዳ የማሰባሰብ፣ የመለየት ብሎም የመቅረፅ ተግባር እንደነበር ይታወቃል፡፡ በተጨማሪም ኮሚሽኑ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን እና ኃላፊነት መሰረት አጀንዳን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት በማሰባሰብ እንዲሁም በሂደቱ የሚሳተፉ ተሳታፊዎችን በመለየት የምክክር ሂደቱን ሲያስተባብር ቆይቷል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ኮሚሽኑ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍን በማጠናቀቅ ወደ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተንደረደረ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ኮሚሽኑ በቅርቡ የሚያስተባብረው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ እስካሁን ከተደረገው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት በምን እንደሚለይ ማወቁ ጠቃሚ ነው፡፡ ኮሚሽኑ አጀንዳን በሰፋፊ ሕዝባዊ ውይይቶች ያሰባሰበበት የምክክር ሂደት የሚከተሉት ቁልፍ ባህሪያት ነበሩት፡፡ ባለድርሻ አካላት እንደሀገር ያልተግባባንባቸውን እጅግ መሰረታዊ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች በውይይት በማዳበር ለኮሚሽኑ አስረክበዋል፤ የብዙ ባለድርሻ አካላት ሕመሞች፣ ሥጋቶች፣ ምኞቶች እና ተስፋዎች በአጀንዳ መልክ ቀርበዋል፤ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለምክክሩ ሂደት የሚጠቅሙ እጅግ በርካታ ግብዓቶችን ሰብስቧል፤ በአንፃራዊነት የተሳታፊዎችን ምቾት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለተሳታፊዎች ቅርብ ናቸው ተብለው በሚታሰቡ ቦታዎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ተከናውኗል፤ በሕዝባዊ ውይይት አጀንዳን የመሰብሰብ ሥራ ብቻውን ሁለት ዓመታትን ፈጅቷል፡፡ በአጠቃላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው መካሄድ እንደ ቅድመ ሁኔታ በማገልገል የራሱን ከፍተኛ ሚና መጫወቱ ቢታወቅም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን የማይተካ መሆኑ ልብ ሊባል ይገባል፡፡ በመሆኑም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የሃሳብ ነፃነትን እና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ማዕከል በማድረግ የባለድርሻ አካላት ወኪሎች በኮሚሽኑ ተቀርፀው በቀረቡ የአጀንዳ ሃሳቦች ላይ መግባባት ላይ ለመድረስ የሚመካከሩበት ጥንቃቄ የተሞላው የምክክር ሂደት ነው፡፡ በምክክር ሂደቱ መግባባት በተደረሰባቸው ሃሳቦች ላይ በመመርኮዝ ምክረ-ሃሳቦች እና የተለያዩ አማራጮች የሚዘጋጁበት ሂደት ነው፡፡ መርሃ-ግብሩ በመዲናችን አዲስ አበባ ይከናወናል፡፡ መርሃ-ግብሩ በየቦታው በተደረጉ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፎች በተሰብሳቢዎች በተመረጡ ተወካዮች ይከናወናል፡፡ መርሃ-ግብሩ ከ4000 በላይ ተሳታፊዎች እንደሚገኙ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
መንግስት ከሚመሰርተው ፓርቲ ጋር ተባብረን በመስራት ለሀገር እድገትና ብልጽግና የበኩላችንን እንወጣለን
Jun 22, 2026 694
ባህር ዳር/ደብረ ብርሃን፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በጠቅላላ ምርጫው አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ በማግኘት አሸናፊ ከሆነው ብልጽግና ፓርቲ ጋር ተባብረን በመስራት ለሀገር እድገትና ብልጽግና የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ የባህር ዳር እና የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተወዳደሩበት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ድምጹን በነጻነት በመስጠት መንግስት ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በምርጫ ብቻ መመስረት እንዳለበት ያለውን ጽኑ ፍላጎቱን አሳይቷል። በዚሁ መሰረት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ መንግስት ለመመስረት የሚያስችለውን አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ ማግኘቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት ይፋ አድርጓል። በምርጫው ውጤት ላይ ኢዜአ በባህር ዳር እና በደብረ ብርሃን ከተማ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች፤ በጠቅላላ ምርጫው አብላጫ መቀመጫ ያገኘው ብልጽግና ፓርቲ በቀጣይ ለህዝብ ዘላቂ ሰላምና ልማት አበክሮ ይሰራል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል። ከምርጫው በፊት ለህዝብ ቃል በገባው መሰረት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮችን ለይቶ መስራት እንዳለበትም ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ ከፓርቲው ጋር ተባብረው በመስራት በሀገር እድገትና ብልጽግና ላይ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ነው ያረጋገጡት። የባህር ዳር ከተማ ነዋሪ አቶ በትግሉ ተስፋሁን እንዳሉት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ያስቻለ እንቅስቃሴ በተግባር ተስተውሏል። በምርጫው አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ በማግኘት አሸናፊ የሆነው ብልጽግና ፓርቲ መንግስት ሲመሰርት ከምርጫ በፊት በገባው ቃል መሰረት ሰላምን ማጽናት እንዳለበት ገልጸዋል። እንዲሁም የህዝብን የላቀ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎችን በማፋጠን የህዝብ አለኝታነቱን ዳግም ማረጋገጥ አለበት ብለዋል። በተመሳሳይ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎችም በምርጫው ካሸነፈው ብልጽግና ፓርቲ ጋር ተባብረው በመስራት በሀገር እድገትና ብልጽግና ላይ የራሳቸውን አሻራ እንደሚያሳርፉ አረጋግጠዋል። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ነዋሪ አቶ ሀብታሙ ሞገስ እንዳሉት፣ በጠቅላላ ምርጫው አብላጫ ድምጽ ያገኘው ብልጽግና ፓርቲ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ማረጋገጥ ላይ አተኩሮ መስራት አለበት። ለምርጫው ያደረጉትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይም ከፓርቲው ጋር በልማት በመተባበር ለሀገር እድገት የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ጊዮርጊስ ቀበሌ ነዋሪ መቶ አለቃ ሰለሞን ዘለቀ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በህዝብ የተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ የተጀመሩ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ዳር ለማድረስ መትጋት አለበት። እርሳቸውም የሚመሰረተው መንግስት የሀገርን ሰላም በዘላቂነት በማረጋገጥ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚያደርገው እንቅስቃሴ ሚናቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። የጠባሴ ክፍለ ከተማ መሳለሚያ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት እጅጋየሁ ሽፈራው በበኩሏ እንዳለችው፤ በህዝብ ድምጽ የተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ ወጣቱን በሥራ ዕድልና በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ የገባውን ቃል በተግባር ማሳየት አለበት። እንደ ወጣትነቷ ባላት እውቀትና ልምድ በፈጠራና በቴክኖሎጂ ላይ አተኩራ በመስራት በሀገር የብልጽግና ጉዞ ላይ አሻራዋን ለማሳረፍ ቁርጠኛ መሆኗን ተናግራለች። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤቶች ብልጽግና ፓርቲ አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ በማግኘት ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው። የምርጫው ውጤት ይፋ መደረጉን ተከትሎም ብልጽግና ፓርቲ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋና ያቀረበ ሲሆን፤ ፓርቲው በቅድመ ምርጫ ለህዝብ የገባውን ቃል ሳይሸራረፍ በመተግበር ሕዝብን በቅንነትና በታማኝነት እንደሚያገለግልም አረጋግጧል ፡፡
አሸናፊ ሆኖ ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲና በምርጫው ለተሳተፋችሁ ሁሉ እንኳን ደስ ያላችሁ -ኢዜማ
Jun 22, 2026 584
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ መሪ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜአ) ገለጸ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው መግለጫው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ በአብዛኛው የምርጫ ክልሎች አሸናፊ መሆኑን ማስታወቁ ይታወሳል። ይሄንን ተከትሎ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ዛሬ ባስተላለፈው መልዕክት ፓርቲው በተወዳደረባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በማግኘቱ ለአባሎቹ እና ለደጋፊዎቹ እንኳን ደስ ያላችሁ ብሏል። በዘንድሮው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባገኘው ውጤትም በሃገር አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን ገልጿል። ስኬቱን ያስመዘገቡ የፓርቲውን ዕጩዎች፣ አባላትና ደጋፊዎችን ያመሰገነው ፓርቲው ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል ክፍተቶቹን በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ዛሬ መሆኑንም ገልጿል። በነዚህ ዓመታት ቀደም ሲል ስናደርገው እንደነበረ ሁሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን በሚያሣኩ ጉዳዮች ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃይል ጋር በመተባበር የምንንቀሳቀስበት ይሆናል ብሏል። መፎካከሪያ አጀንዳዎች ላይ ማኅበረሰባችንን በሚመጥን ጨዋነት ልዩነቶቻችንንና ትችቶቻችንን እያቀረብን የጀመርነውን ጤናማና ዘመናዊ የፖለቲካ ባሕል የማዋለድ ተግባራችንን በተጠናከረ መልኩ የምንቀጥልበት እንዲሁም ለተጨማሪ ስኬት የምንንደረደርበት እንደሚሆን ቃል እንገባለን ሲልም ገልጿል። ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን ብሏል ፓርቲው በመልዕክቱ። አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ ለሀገር እድገትና ለውጥ ጠቃሚ ሀሳቦች ከማንኛውም ወገን ሊገኙ እንደሚችሉ በመረዳት አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ ጠይቋል። እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ ሀገራችን የሚያስፈልጋትን ዴሞክራሲ በጋራ እንድንገነባ ጥሪ እናቀርባለን ሲልም ኢዜማ ባስተላለፈው መልዕክት ገልጿል።
ፖለቲካ
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ
Jun 22, 2026 820
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ (ዶ/ር)ን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ውይይቱን አስመልክቶ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡   ውይይቱ ኢትዮጵያ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ስደተኞችን በማስተናገድ ረገድ ለምትጫወተው ወሳኝ ሚና ድርጅታቸው ያለውን አድናቆትና እውቅና ለመግለጽ ትልቅ አጋጣሚ መፍጠሩን ገልጸዋል። በተለይም ሀገሪቱ ስደተኞችን በብሔራዊ ሥርዓቱ ውስጥ ለማካተትና በሰብአዊ እርዳታ ላይ ብቻ ጥገኞች እንዳይሆኑ ለመርዳት በቅርቡ ይፋ ያደረገችውን የማካተት ፍኖተ ካርታን በአብነት ጠቅሰዋል። በፍኖተ ካርታው የትግበራ ሂደት ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም የጋራ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል፣ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ ኢትዮጵያ በቅርቡ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት በማጠናቀቋ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው፤ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክትም አስተላልፈዋል።
የብልፅግና ፓርቲ የሀገሪቱን ልማት ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ የጋራ ምክር ቤቱ አብሮ ለመሥራት ዝግጁ ነው
Jun 22, 2026 672
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የምርጫ አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ የከተማዋንና የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ፣ የጋራ ምክር ቤቱ በነቃ ተሳትፎ፣ በገንቢ ሂስና በአማራጭ ሃሳቦች አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቅን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። የጋራ ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተጠናቆ የብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ በማግኘት ማሸነፉን አስታውቋል። ምክር ቤቱ ይህ ምርጫ የከተማዋንና የሀገሪቱን የፖለቲካ ብስለት እንዲሁም የሕዝብን የሉዓላዊነት ስልጣን ያረጋገጠ ታሪካዊ መድረክ መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን ገልጾ፣ በሕዝብ ነፃ ውሳኔ አሸናፊ ለሆነው ለብልፅግና ፓርቲ እና በውድድሩ ተሳትፈው የምክር ቤት ወንበር ላገኙ ፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ምክር ቤቱ ስም ልባዊ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ታሪካዊው ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅና የዲሞክራሲ ባህል እንዲጎለብት በውድድሩ የተሳተፉ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ላበረከቱት አዎንታዊና ታሪካዊ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ የላቀ ምስጋና አቅርቧል። በምክር ቤቱ ስር የሚንቀሳቀሱም ሆኑ በምርጫው የተሳተፉ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሂደቱ ላሳዩት ከፍተኛ የፖለቲካ ጨዋነት፣ለሰላማዊ የሃሳብ ፉክክርና ለሕግ የበላይነት መገዛት የሚደነቅ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው፣ይህ የሰለጠነ አካሄድ ለዜጎች ሰፊ የአማራጭ አድማስ ከመፍጠሩም በላይ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ቁልፍ ሚና መጫወቱን አስገንዝቧል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በነፃነትና በሰላማዊ መንገድ ወጥተው የሰጡትን ድምፅና ያሳዩትን ምርጫ በሙሉ ልብ በመቀበል፣ ለሕዝብ ድምፅ ያለውን ፍጹም ክብርና እውቅና አረጋግጧል። የምርጫው ምዕራፍ በተሳካ ሁኔታ ቢጠናቀቅም፣የሀገር ግንባታ እና የሕዝብ አገልግሎት ቀጣይነት ያለው የጋራ ሃላፊነት በመሆኑ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ምክር ቤቱ አሳስቧል። አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ የከተማዋንና የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ፣ የጋራ ምክር ቤቱ በነቃ ተሳትፎ፣ በገንቢ ሂስና በአማራጭ ሃሳቦች አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ምክር ቤቱ በውድድሩ ተሳትፈው የምክር ቤት ወንበር ላገኙ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች፣ እንዲሁም በድጋሚ ለብልፅግና ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች እንኳን ደስ ያላችሁ ብሏል። መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ባለድርሻ አካላት ለሰላማዊው የምርጫ ሂደት ስኬት ላደረጉት ታሪካዊ አስተዋጽኦም ምስጋናውን አቅርቧል።
የኢትዮጵያ እና የዩናይትድ ኪንግደም ግንኙነት ይበልጥ ሊጠናከር ይገባል-ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Jun 22, 2026 611
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የኢትዮጵያና የዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል። በለንደን ከተማ የሲዳራ ግሩፕ (Sidara Group) ያዘጋጀው እንዲሁም በሌበር አፍሪካ ኔትወርክ (Labour African Network) እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም ኤምባሲ በጋራ በተሰናዳው የዲፕሎማቲክ እራት መርሐ ግብር ተካሄዷል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም የዕድገትና ብልጽግና አዳዲስ ዕድሎችን ለመጠቀም የውይይት እና የትብብር መድረኮች ወሳኝ ሚና አላቸው። የኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም ግንኙነት በመንግሥት ተቋማት መካከል ብቻ የተገደበ እንዳልሆነ ገልጸዋል። ትብብሩ በንግድ ድርጅቶች፣ በትምህርት ተቋማት፣ በዲያስፖራ ማህበረሰቦች እና በሁለቱ ሀገራት ዜጎች መካከል ባለው ዘላቂ ትስስር ላይ የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትም ለጠንካራ እና ዘላቂ አጋርነት ዋነኛው ምሰሶ ነው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ወቅታዊ የሪፎርም አጀንዳ እና የረጅም ጊዜ የልማት ትልሞችን አንስተዋል። በተለይም ኢኮኖሚውን ለማጠናከር፣ ለወጣቱ ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንዲሁም አካታች እና ዘላቂ ዕድገትን ለማስፈን እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን አንስተዋል።   የኢትዮጵያን ሕዝብ የአይበገሬነት አቅምና በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለውን አዲስ የተስፋ መንፈስ በመጥቀስም የወደፊቱ ጊዜ ብሩህ እንደሚሆን ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል በንግድ፣በኢንቨስትመንት፣በትምህርት፣ በምርምር፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራ (ኢኖቬሽን) እና በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም አቅም ዙሪያ ሰፊ የትብብር ዕድሎች መኖራቸውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰበ የመጣውን ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ በአግባቡ ለመወጣት እና ለሁለቱም ሀገራት ዜጎች ተጨባጭ ጥቅሞችን ለማስገኘት ጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት መፍጠር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም አሳስበዋል።   የሌበር አፍሪካ ኔትወርክ (LAN) ሊቀመንበር ኤርነስት አምቤ በንግግራቸው ኔትወርኩ፤ የአፍሪካ ድምጽ በዩናይትድ ኪንግደም የፖሊሲ ቀረጻ፣ የንግድ እና የዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ ጎልቶ እንዲሰማ በማድረግ ረገድ የተጫወተውን ጉልህ ሚና አድንቀዋል። አያይዘውም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከአፍሪካ ትላልቅ እና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ገበያዎች አንዱ መሆኑን በልዩ ሁኔታ አንስተዋል። በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን በበኩላቸው፥ የዲፕሎማሲ ሁነቱ እየተጠናከረ የመጣው የሀገራቱ የንግድ፣የኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ትብብር ለማስፋት መልካም አጋጣሚን መፍጠሩን ገልጸዋል።   ዩናይትድ ኪንግደም ከኢትዮጵያ እና ከአጠቃላይ አፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ አጋርነት ማደግ አዳዲስ ዕድሎችን፣ የጋራ ብልጽግናን እና አካታች ዘላቂ ዕድገትን ለማምጣት እንደሚያስችል መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ብልፅግና ፓርቲ በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Jun 22, 2026 544
ጅማ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ይፋ ባደረገው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት፣ ብልፅግና ፓርቲ በአብላጫ የምርክ ቤት መቀመጫ ማግኘቱ ይታወቃል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ታመነ ኃይሉ፤ ፓርቲው የጀመራቸውን ትልልቅ ፕሮጀክቶችና በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ፓርቲው ከዚህ ቀደም ያከናወናቸው ሰው-ተኮር ልማቶች አገሪቱን ከድህነት ለማውጣት ከፍተኛ አቅም ማበርከታቸውን የጠቀሱት አቶ ታመነ፤ በቀጣይም ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ርብርብ ሕዝቡና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ ይሰራሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሙደሲር መሐመድ በበኩላቸው፤ ፓርቲው ያቀዳቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ለሕዝብ ተጠቃሚነት ለማዋል ከታችኛው መዋቅር ጀምሮ ሙስናን የመታገል ተግባሩን ማጠናከር እንዳለበት ጠቁመዋል። ለዚህም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አሰራር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት፣ የሙስና መከላከያ ስልቶችን ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል። የአገርን ሰላም ማስከበርና ልማትን ማፅናት ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም ያሉት አቶ ሙደሲር፤ ጉዳዩ የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ እሳቸውም የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ሕዝቡ በምርጫ ሥልጣን የሰጠው ፓርቲ የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠርና ሕገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል የሚያደርገውን ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ደግሞ አቶ መልካሙ ቡላ እና አቶ በፀጋው አበራ ናቸው። አስተያየት ሰጪዎቹ የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ማንኛውንም ጥረት በንቃት በመደገፍ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አስታውቀዋል።
ምርጫው ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው-አብን
Jun 22, 2026 558
አዲስ አበባ፤ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፡-7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው ሲል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ገለጸ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ትናንት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫውን ሂደት ስኬታማነት በመግለጽ፤ ውጤቱን በጸጋ መቀበላቸውን እና በአብላጫ ድምጽ ላሸነፈው ብልጽግና ፓርቲም የመልካም ምኞት መግለጫ እያስተላለፉ ነው። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በበኩሉ ባወጣው መግለጫም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው ብሏል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ ወደ ተሻለ የፖለቲካ እና የማኅበረ-ኢኮኖሚ ምዕራፍ ለመሻገር ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ውሳኔ መሆኑንም አመላክቷል። የተመዘገበው ስኬት የማህበረሰባችን የአርቆ አሳቢነት ትሩፋት በመሆኑ ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባም ነው ብሏል በመግለጫው፡፡ ምርጫው ሕዝባችን ፈተናዎችን ተቋቁሞ በታሪክ የሚዘከር የአይበገሬነት ታሪክ የጻፈበት፣ ለዘላቂ ሰላምና እድገት የሚበጅ የፖለቲካ ባህል አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ ያደረገበት፣ በዋናነት የማኅበረ-ፖለቲካ ግብረ-ገብ እሴቶች ተቃራኒ የሆኑ ጯሂና እኩይ ድምጸቶችን ማሸነፍ የቻለበት፣ ለሰላም ሲባል ዋጋ የመክፈል ቁርጠኝነት የታየበትና ዋጋ የተከፈለበት መሆኑንም ነው የገለጸው። ሕዝብን ማሸነፍ አይቻልምና ድሉ የሰላም ወዳዱ ሕዝብ ሆኗልም ነው ያለው። ምርጫው ለውጫዊ የኢትዮጵያ ጠላቶችም ተስፋ ያስቆረጠ ክስተት መሆኑንም አብን ገልጿል። ዳያስፖራው ልማቶችንና የሰላም እንቅስቃሴዎችን እንዲደግፍ እንዲሁም ለሀገራዊ መረጋጋት ፋይዳ ከሌላቸው አጀንዳዎች ራሱን እንዲያርቅ አብን ጥሪ አቅርቧል። በመጨረሻም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምጽ ላገኘው ብልጽግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልካም ምኞቱን ገልጾ፤መጭው ጊዜ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ሁለንተናዊ ምዕራፍ የምናሻግርበት ነው ሲል ገልጿል።
የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሌሎች የምክክር ሂደቶች በምን ይለያል?
Jun 22, 2026 652
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክሩን ለማስተባበር ሥራውን ሲጀምር በስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ካስቀመጣቸው ምሰሶዎች አንዱና ዋነኛው አጀንዳ የማሰባሰብ፣ የመለየት ብሎም የመቅረፅ ተግባር እንደነበር ይታወቃል፡፡ በተጨማሪም ኮሚሽኑ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን እና ኃላፊነት መሰረት አጀንዳን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት በማሰባሰብ እንዲሁም በሂደቱ የሚሳተፉ ተሳታፊዎችን በመለየት የምክክር ሂደቱን ሲያስተባብር ቆይቷል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ኮሚሽኑ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍን በማጠናቀቅ ወደ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተንደረደረ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ኮሚሽኑ በቅርቡ የሚያስተባብረው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ እስካሁን ከተደረገው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት በምን እንደሚለይ ማወቁ ጠቃሚ ነው፡፡ ኮሚሽኑ አጀንዳን በሰፋፊ ሕዝባዊ ውይይቶች ያሰባሰበበት የምክክር ሂደት የሚከተሉት ቁልፍ ባህሪያት ነበሩት፡፡ ባለድርሻ አካላት እንደሀገር ያልተግባባንባቸውን እጅግ መሰረታዊ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች በውይይት በማዳበር ለኮሚሽኑ አስረክበዋል፤ የብዙ ባለድርሻ አካላት ሕመሞች፣ ሥጋቶች፣ ምኞቶች እና ተስፋዎች በአጀንዳ መልክ ቀርበዋል፤ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለምክክሩ ሂደት የሚጠቅሙ እጅግ በርካታ ግብዓቶችን ሰብስቧል፤ በአንፃራዊነት የተሳታፊዎችን ምቾት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለተሳታፊዎች ቅርብ ናቸው ተብለው በሚታሰቡ ቦታዎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ተከናውኗል፤ በሕዝባዊ ውይይት አጀንዳን የመሰብሰብ ሥራ ብቻውን ሁለት ዓመታትን ፈጅቷል፡፡ በአጠቃላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው መካሄድ እንደ ቅድመ ሁኔታ በማገልገል የራሱን ከፍተኛ ሚና መጫወቱ ቢታወቅም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን የማይተካ መሆኑ ልብ ሊባል ይገባል፡፡ በመሆኑም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የሃሳብ ነፃነትን እና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ማዕከል በማድረግ የባለድርሻ አካላት ወኪሎች በኮሚሽኑ ተቀርፀው በቀረቡ የአጀንዳ ሃሳቦች ላይ መግባባት ላይ ለመድረስ የሚመካከሩበት ጥንቃቄ የተሞላው የምክክር ሂደት ነው፡፡ በምክክር ሂደቱ መግባባት በተደረሰባቸው ሃሳቦች ላይ በመመርኮዝ ምክረ-ሃሳቦች እና የተለያዩ አማራጮች የሚዘጋጁበት ሂደት ነው፡፡ መርሃ-ግብሩ በመዲናችን አዲስ አበባ ይከናወናል፡፡ መርሃ-ግብሩ በየቦታው በተደረጉ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፎች በተሰብሳቢዎች በተመረጡ ተወካዮች ይከናወናል፡፡ መርሃ-ግብሩ ከ4000 በላይ ተሳታፊዎች እንደሚገኙ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
መንግስት ከሚመሰርተው ፓርቲ ጋር ተባብረን በመስራት ለሀገር እድገትና ብልጽግና የበኩላችንን እንወጣለን
Jun 22, 2026 694
ባህር ዳር/ደብረ ብርሃን፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በጠቅላላ ምርጫው አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ በማግኘት አሸናፊ ከሆነው ብልጽግና ፓርቲ ጋር ተባብረን በመስራት ለሀገር እድገትና ብልጽግና የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ የባህር ዳር እና የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተወዳደሩበት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ድምጹን በነጻነት በመስጠት መንግስት ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በምርጫ ብቻ መመስረት እንዳለበት ያለውን ጽኑ ፍላጎቱን አሳይቷል። በዚሁ መሰረት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ መንግስት ለመመስረት የሚያስችለውን አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ ማግኘቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት ይፋ አድርጓል። በምርጫው ውጤት ላይ ኢዜአ በባህር ዳር እና በደብረ ብርሃን ከተማ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች፤ በጠቅላላ ምርጫው አብላጫ መቀመጫ ያገኘው ብልጽግና ፓርቲ በቀጣይ ለህዝብ ዘላቂ ሰላምና ልማት አበክሮ ይሰራል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል። ከምርጫው በፊት ለህዝብ ቃል በገባው መሰረት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮችን ለይቶ መስራት እንዳለበትም ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ ከፓርቲው ጋር ተባብረው በመስራት በሀገር እድገትና ብልጽግና ላይ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ነው ያረጋገጡት። የባህር ዳር ከተማ ነዋሪ አቶ በትግሉ ተስፋሁን እንዳሉት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ያስቻለ እንቅስቃሴ በተግባር ተስተውሏል። በምርጫው አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ በማግኘት አሸናፊ የሆነው ብልጽግና ፓርቲ መንግስት ሲመሰርት ከምርጫ በፊት በገባው ቃል መሰረት ሰላምን ማጽናት እንዳለበት ገልጸዋል። እንዲሁም የህዝብን የላቀ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎችን በማፋጠን የህዝብ አለኝታነቱን ዳግም ማረጋገጥ አለበት ብለዋል። በተመሳሳይ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎችም በምርጫው ካሸነፈው ብልጽግና ፓርቲ ጋር ተባብረው በመስራት በሀገር እድገትና ብልጽግና ላይ የራሳቸውን አሻራ እንደሚያሳርፉ አረጋግጠዋል። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ነዋሪ አቶ ሀብታሙ ሞገስ እንዳሉት፣ በጠቅላላ ምርጫው አብላጫ ድምጽ ያገኘው ብልጽግና ፓርቲ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ማረጋገጥ ላይ አተኩሮ መስራት አለበት። ለምርጫው ያደረጉትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይም ከፓርቲው ጋር በልማት በመተባበር ለሀገር እድገት የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ጊዮርጊስ ቀበሌ ነዋሪ መቶ አለቃ ሰለሞን ዘለቀ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በህዝብ የተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ የተጀመሩ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ዳር ለማድረስ መትጋት አለበት። እርሳቸውም የሚመሰረተው መንግስት የሀገርን ሰላም በዘላቂነት በማረጋገጥ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚያደርገው እንቅስቃሴ ሚናቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። የጠባሴ ክፍለ ከተማ መሳለሚያ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት እጅጋየሁ ሽፈራው በበኩሏ እንዳለችው፤ በህዝብ ድምጽ የተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ ወጣቱን በሥራ ዕድልና በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ የገባውን ቃል በተግባር ማሳየት አለበት። እንደ ወጣትነቷ ባላት እውቀትና ልምድ በፈጠራና በቴክኖሎጂ ላይ አተኩራ በመስራት በሀገር የብልጽግና ጉዞ ላይ አሻራዋን ለማሳረፍ ቁርጠኛ መሆኗን ተናግራለች። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤቶች ብልጽግና ፓርቲ አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ በማግኘት ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው። የምርጫው ውጤት ይፋ መደረጉን ተከትሎም ብልጽግና ፓርቲ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋና ያቀረበ ሲሆን፤ ፓርቲው በቅድመ ምርጫ ለህዝብ የገባውን ቃል ሳይሸራረፍ በመተግበር ሕዝብን በቅንነትና በታማኝነት እንደሚያገለግልም አረጋግጧል ፡፡
አሸናፊ ሆኖ ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲና በምርጫው ለተሳተፋችሁ ሁሉ እንኳን ደስ ያላችሁ -ኢዜማ
Jun 22, 2026 584
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ መሪ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜአ) ገለጸ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው መግለጫው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ በአብዛኛው የምርጫ ክልሎች አሸናፊ መሆኑን ማስታወቁ ይታወሳል። ይሄንን ተከትሎ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ዛሬ ባስተላለፈው መልዕክት ፓርቲው በተወዳደረባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በማግኘቱ ለአባሎቹ እና ለደጋፊዎቹ እንኳን ደስ ያላችሁ ብሏል። በዘንድሮው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባገኘው ውጤትም በሃገር አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን ገልጿል። ስኬቱን ያስመዘገቡ የፓርቲውን ዕጩዎች፣ አባላትና ደጋፊዎችን ያመሰገነው ፓርቲው ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል ክፍተቶቹን በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ዛሬ መሆኑንም ገልጿል። በነዚህ ዓመታት ቀደም ሲል ስናደርገው እንደነበረ ሁሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን በሚያሣኩ ጉዳዮች ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃይል ጋር በመተባበር የምንንቀሳቀስበት ይሆናል ብሏል። መፎካከሪያ አጀንዳዎች ላይ ማኅበረሰባችንን በሚመጥን ጨዋነት ልዩነቶቻችንንና ትችቶቻችንን እያቀረብን የጀመርነውን ጤናማና ዘመናዊ የፖለቲካ ባሕል የማዋለድ ተግባራችንን በተጠናከረ መልኩ የምንቀጥልበት እንዲሁም ለተጨማሪ ስኬት የምንንደረደርበት እንደሚሆን ቃል እንገባለን ሲልም ገልጿል። ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን ብሏል ፓርቲው በመልዕክቱ። አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ ለሀገር እድገትና ለውጥ ጠቃሚ ሀሳቦች ከማንኛውም ወገን ሊገኙ እንደሚችሉ በመረዳት አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ ጠይቋል። እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ ሀገራችን የሚያስፈልጋትን ዴሞክራሲ በጋራ እንድንገነባ ጥሪ እናቀርባለን ሲልም ኢዜማ ባስተላለፈው መልዕክት ገልጿል።
ማህበራዊ
ባለስልጣኑ የትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነቱን ማስፋፋትና አቅሙን ማጠናከር አለበት
Jun 22, 2026 425
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነቱን ማስፋፋትና አቅሙን ማጠናከር እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት የአስራ አንድ ወራት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል። የቋሚ ኮሚቴው አባላት ባለስልጣኑ ዓለም አቀፍ እውቅናን ለማግኘት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትና ሌሎች ሥራዎች በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ጠይቀዋል፡፡ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አሕመድ አብተው (ዶ/ር) ባለፉት ዓመታት የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በተከናወኑ ተግባራት የትምህርት ተቋማት ጥራት ላይ ሰፊ ለውጥ መመዝገቡን አመላክተዋል፡፡ የአካዳሚክ ጥራት ኦዲት፣ የክትትልና ቁጥጥር፣ የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ፣ የአቻ ግመታ መመሪያዎችና ስታንዳርዶች ሥራ ላይ በመዋላቸው የባለስልጣኑ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እያደገ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዘገባ ስርዓት ውስጥ እንዲገቡ መደረጉንም አክለዋል። የትምህርት ዘርፍ ፍቃድ እና የፍቃድ ዕድሳት እንዲደረግላቸው ለጠየቁ ለዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች ተገቢውን የጥራት መመዘኛ በማድረግ ፍቃድ መሰጠቱንም ገልጸዋል። የአጠቃላይ የትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነት ለማስፋፋትም የክልሎችን አቅም የማጎልበት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ባለስልጣኑ ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎች እውቅና ለማግኘት የሰነድና ሌሎች ዝግጅቶች እየያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፣ በባለስልጣኑ የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል፡፡ ሪፎርሙ በትምህርት ጥራነትና አግባብነትን ላይ ተጨባጭ ውጤት ማመጣቱንና የትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነት እንዲሰፋ ማስቻሉን ነው ያነሱት። በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የተገልጋዮች እርካታ፣ የአካዳሚክ ጥራት ኦዲት እና በትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተደራሽነት ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ባለስልጣኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኝ በማድረግ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ ፕሮግራሞች በሀገርና በዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኙ ማድረግና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራትን መደገፍ ይገባል ብለዋል። ቋሚ ኮሚቴው አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡      
በክልሉ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የመደጋገፍ ማህበራዊ እሴቶችን አሳድጓል -ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
Jun 22, 2026 262
አሶሳ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ችግሮች ከመፍታት ባለፈ የመደጋገፍ ማህበራዊ እሴቶችን ማሳደጉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ። የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች ዙሪያ ተወያይተዋል። ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ የበጎ ፍቃድ ተግባራት በየጊዜው እያደጉ በመምጣታቸው የህዝቡን የልማትና ማህበራዊ አገልግሎቶች ለማሳለጥ እያገዙ ናቸው። ተግባሩ የመንግስትን በጀት ከመቆጠቡ ባለፈ የህብረተሰቡን የመረዳዳት ማህበራዊ እሴት እንዲያድግ ማገዙን አስረድተዋል። ለአብነትም በክልሉ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የቤት ግንባታ፣ የአረንጓዴ አሻራ እንዲሁም ሌሎች አገልግሎቶች የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ እና የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ ያሳዩ እንደነበሩ አስታውሰዋል። ተግባሩ የመንግስትን ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ከማሳደጉ ባለፈ አቅም ለሌላቸው ማህበረሰቦች አለኝታ መሆን እንደቻለም ተናግረዋል። በቀጣይም ወጣቶችና የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የበጎ ፍቃድ አገልግሎትን ለማስፋት ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል። የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አለምነሽ ይባስ በበኩላቸው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ችግር ከማቃለል ባለፈ ማህበራዊ ትስስርን ማጠናከር እና መተጋገዝ እንዲጎለብት ሚናውን ተወጥቷል ብለዋል። የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱን በዘንድሮው የክረምት ወራት በማስቀጠል ከ984 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ ተግባራት እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል። በተግባሩ ከሚከናወኑ 14 ዋና ዋና አገልግሎቶች ውስጥ የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ አረንጓዴ አሻራና ደም ልገሳ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። በመርሀ ግብሩ ከ502 ሺህ በላይ በጎ ፍቃደኞች እንደሚሳተፉም አስታውቀዋል።
ዩኒቨርሲቲው በእውቀትና በክህሎት የበለጸገ የሰው ሃይል በማፍራት ረገድ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ ነው
Jun 22, 2026 247
ደሴ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፡- የወሎ ዩኒቨርሲቲ በእውቀትና በክህሎት የበለጸገ የሰው ሃይል በማፍራት ረገድ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ መሆኑን ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው የተግባር ተኮር ትምህርትን ውጤታማ ለማድረግ የቀረጻቸው የስርዓተ-ትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው።   የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፣ ዩኒቨርሲቲው ተግባር ተኮር ስርዓተ ትምህርትን ውጤታማ ለማድረግ መሰረተ ልማትና ግብዓት ማሟላት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው። ለዚህም በጥናት በለያቸው 44 ፕሮግራሞች ላይ የሚመክር መድረክ ዛሬ በማዘጋጀት ግብዓትን በማሰባሰብ አዳብሮ በ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ስራው ላይ ለመተግበር ማለሙን ጠቁመዋል። የፕሮግራሞቹ ትግበራም በእውቀትና በክህሎት የበለጸገ የሰው ሃይል በማፍራት ረገድ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እንደሚያግዙት አረጋግጠዋል። ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራቱን በማስጠበቅ ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማት አዎንታዊ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ትውልድ ለመገንባት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   በዩኒቨርሲቲው የጢጣ ልዕለ ህክምና ካምፓስ የፋርማሲ ትምህርትና አገልግሎት ትምህርት ክለሳ ኮሚቴ ሰብሳቢ አድማሱ አሰን (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ተግባር ተኮር ትምህርትን እውን ለማድረግ የፕሮግራም ክለሳ ተካሄዷል። በጤናው ዘርፍም አገልጋይነትን የተላበሰ ባለሙያ በማፍራት ጤንነቱ የተጠበቀ፣ አምራች፣ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለመፍጠር እንደሚያስችልም አስገንዝበዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ድንኳና ንጉሣ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅ ብቁ የሰው ሃይል ለማፍራት መሰረታዊ ጉዳይ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።   በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመሩ ማሻሻያዎች የትምህርት ስርዓቱን ተግባር ተኮር ማድረግና ለጥራት ትኩረት በመስጠት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እየተሰራ ነው ያሉት።    
የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ችግርን ለማቃለል በቅንጅት መስራት ይገባል
Jun 22, 2026 215
ባህር ዳር፤ ሰኔ 15 /2018 (ኢዜአ)፡-የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለማቃለል በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ አመለከተ። የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲና የአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በመተባበር "የዓለም የምግብ ቀንን" ዛሬ በባህር ዳር ከተማ አክብረዋል። በዩኒቨርሲቲው የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ስራ አስፈጻሚ በቃሉ ውብሸት (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ የስነ- ምግብ ጉዳይ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅትና ትብብር የሚጠይቅ ነው።   ዩኒቨርሲቲውም የተመጣጠነ ምግብ እጥረት የሚያስከትለውን ጉዳት ቀድሞ በመገንዘብ ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራትና በዘርፉ ምርምሮችን በማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከዚህ ውስም የግብርናውን ዘርፍ በመደገፍ የሰብል ምርቶች በዓይነትና በብዛት እንዲመረቱ በማድረግም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሚገኝ አመላክተዋል። የመድረኩ ዋና ዓላማም የምርምር ስራዎችን አጠናክሮ ከማስቀጠል ባለፈ በምግብ እጥረት የሚመጡ የጤና ችግሮችን ለማቃለል የተሻሉ ስራዎችን ለመስራት ያለመ ነው ብለዋል። የአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በምርምር የታገዘና መረጃን መሠረት ያደረጉ ችግር ፈቺ የፖሊሲ ምክረ-ሀሳቦችን በማቅረብ የጤና ችግሮች እንዲፈቱ እየሰራ ይገኛል።   በክልሉ የህጻናት መቀንጨር ችግርን ለመቅረፍም ከምርት ጀምሮ እስከ አመጋገብ ያለውን ችግር ለመፍታት ግንዛቤ ፈጠራ ላይ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። እንደ ሀገር በግብርናው ዘርፍ የተያዘውን በምግብ ራስን የመቻል ግብ ለማሳካት የምርምር ስራዎችን በማስፋት ማከናወን እንደሚገባ ነው ያመለከቱት። የስርዓተ-ምግብ ጉዳይ የተፈጥሮና የሰብዓዊ መብት ጉዳይ በመሆኑ፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ መንግስታዊና ሌሎች ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ችግሩን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ሁሉ እገዛ እንዲያደርጉም አሳስበዋል። በመድረኩ ላይም የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ የአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አመራሮች፣ ተመራማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያን የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብቶች ምርታማነት የማሳደግ የዝርያ ማሻሻል ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
Jun 22, 2026 510
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ):- የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ዝርያን የሚያሻሽሉ ሙያተኞችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል። በዚህም ኢንስቲትዩቱ ከሰኔ 08 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በሰው ሰራሽ ማዳቀል የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ዝርያን ለማሻሻል ለሙያተኞች የሰጠውን ስልጠና በማጠናቀቅ ሰልጣኞችን አስመርቋል። የግብርና ሚንስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ፤ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ያላት ሀገር ናት ብለዋል። የኢትዮጵያን የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ለማሻሻልም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችንና የአሰራር ሥርዓቶችን በመቅረፅ እየተሰራባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ለማሻሻል እየተሰራበት የሚገኘው የሰው ሰራሽ ማዳቀል ሥነ-ዘዴ ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩትም የሰው ሰራሽ ማዳቀል ሙያተኞችን በብዛትና በጥራት ለማፍራት መሰረት መጣሉን አንስተዋል። በኢንስቲትዩቱ ትምህርትና ስልጠና የተሰጣቸው ሙያተኞችም የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን በማሻሻል ህዝባቸውን ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የመደመር መንግሥት የገጠር ሽግግርን ለማሳለጥ ለእንስሳት ሃብት ምርታማነት ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸዋል። በዚህም የመንግሥትን መርህ ታሳቢ በማድረግ በሰው ሰራሽ የማዳቀል ሥነ-ዘዴ የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትና ጤንነት ሙያተኞችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ለምርቃት ለበቁት ሰልጣኝ ሙያተኞችም በእንስሳት እንክብካቤና አመጋገብ፣ በሽታ መከላከልና ጤና አጠባበቅ፣ ምርት ማቀነባበሪያና የገበያ ትስስር ትምህርት መሰጠቱን አስረድተዋል። በስልጠናውም የያቤሎ፣ ጂንካ፣ ባኮ፣ አዳሚቱሉ፣ የዓርባ ምንጭ ምርምር ማዕከላት፣ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት እንዲሁም የግል እርሻ ሙያተኞች መሳተፋቸውን አስረድተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ስንዴን በኩታ ገጠም በማልማታችን ኑሯችን እየተሻሻለ መጥቷል-  አርሶ አደሮች 
Jun 22, 2026 225
አምቦ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ስንዴን በኩታ ገጠም ማልማት ከጀመሩ ወዲህ ኑሯቸው እየተሻሻለ መምጣቱን በምዕራብ ሸዋ ዞን የወልመራ ወረዳ አርሶአደሮች ተናገሩ፡፡ በዞኑ ወልመራ ወረዳ የመኸር ኩታ ገጠም ስንዴ ልማት ዘር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የዞኑ እና የወረዳው የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተካሄዷል፡፡ በወቅቱ ኢዜአ ያነጋገራቸው የወረዳው አርሶአደሮች ባለፉ ዓመታት ስንዴን በኩታ ገጠም በማልማት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣታቸውን ገልጸዋል፡፡ ከአርሶ አደሮቹ መካከል ነገሰ ለታ እንደገለጹት ባለፉት ሶስት ዓመታት ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በመደራጀት በኩታ ገጠም ስንዴን እያለሙ ነው፡፡ ስንዴን በኩታ ገጠም ማልማታቸው ከዚህ በፊት ከአንድ ሄክታር ያገኙት የነበረውን 20 ኩንታል ምርት አሁን ላይ ወደ 40 ኩንታል ማድረስ እንደቻሉ ተናግረዋል። የስንዴን ምርታማነት ለማሳደግም ግብአትን በአግባቡ መጠቀምና ከወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች ሙያዊ ድጋፍ ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። ሌላው አርሶ አደር ደንደና ከበደ በበኩላቸው በመኸር እርሻ ከስንዴ ልማታቸው የተሻለ ምርት ለማግኘት በኩታ ገጠም ማረሳቸውን ተናግርዋል። የባለፉት አመታት የኩታገጠም እርሻ የተሻለ ምርት ለማግኘት እንደረዳቸው ጠቁመው ዘንድሮም ተግባሩን ለማስቀጠል እየተጉ መሆናቸውን ገልጸዋል ። ከአካባቢያቸው አርሶአደሮች ጋር በኩታ ገጠም ማረሳቸው ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው ባለፈ በማህበራዊ ኑሯቸው ላይም ለውጥ ማምጣቱን አስረድተዋል፡፡ የወረዳው ግብርና ጽፈት ቤት የግብርና ግብአት በወቅቱ ማቅረቡም ለምርታማነታቸው ማገዙን ጠቅሰዋል። የወልመራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጋሪ በበኩላቸው፤ በወረዳው የአርሶአደሮችን ምርታማነት በማሳደግ ከተረጅነት ለማውጣት በቅንጅት መሰራቱን ጠቁመዋል። ለዚህም ለአርሶ አደሩ ግብአትና ሙያዊ ድጋፍን በማቅረብ በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ የቁጣባ ባህሉ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ በዘንድሮ መኸር እርሻ በወረዳው ከ34 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 18 ሺህ ሄክታሩ በስንዴ እንደሚለማ ተናግረዋል። ከስንዴ ልማቱም 900 ሺህ ኩንታል ምርት ለማገኘት ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መርጋ አየለ፤ በዞኑ በመኸር እርሻ ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን ታቅዷል ብለዋል። በመኸር አዝመራው በቆሎ፣ ማሽላ እና ስንዴ በኩታ ገጠም እንደሚለሙ ጠቁመው ከዚህም ውስጥ ከ232 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ለማልማት መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ማሳድግ መቻሉን የገለጹት ደግም የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አበበ ጨመዳ ናቸው። የግብርናውን ውጤታማነት ለማሳደግ ለግብርና ቴክኖሎጂና ግብአት አቅርቦት ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። የአርሶ አደሩን የኩታ ገጠም አስተራረስ ግንዛቤ በማጎልበት ምርታማነቱን በማሳድግ ከፍጆታው አልፎ ለገበያ የሚያቀርብበትን አቅም ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
የመስኖ ፕሮጀክቶችን በጥራትና ፍጥነት በማጠናቀቅ የልማት አቅም ለማድረግ የስታንዳርድ አሰራሮች ስራ ላይ ውለዋል
Jun 22, 2026 496
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በጥራትና ፍጥነት በማጠናቀቅ የልማት አቅም ለማድረግ የሚያስችሉ የስታንዳርድ አሰራሮች ስራ ላይ ማዋሉን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱረህማን አብደላ ገለፁ። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከክልል መስኖ ቢሮ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በውስጥ ስታንዳርድ ዝግጅትና ትግበራ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሂዷል።   የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱረህማን አብደላ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፣ አዲሱ ስታንዳርድ እያንዳንዳቸው የመስኖ ፕሮጀክቶች የሚያልፉበትን ሂደት በግልጽ ያስቀምጣል። ስታንዳርዱ በፌደራል ደረጃ ብቻ ሳይሆን በክልሎችም በሚገነቡ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ጭምር ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል። በትግበራው አማካኝነት ትልቁ የመስኖ ፕሮጀክቶች ፈተና የሆነው የዲዛይንና ጥናት ችግር ከስር መሰረቱ እንደሚፈታ ጠቁመዋል።   የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የመስኖ ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን መሪ ሰራ አስፈፃሚ ያሬድ ሙላት፣ ሰነዱን ሙሉ በሙሉ በውስጥ አቅም የተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ስታንዳርዱ ከህዳር 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ወደ ትግበራ መግባቱን አስታውቀዋል። በዚህም በመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ከዚህ ቀደም ይነሱ የነበሩ የጥራትና የዲዛይን ለውጥ ጥያቄዎች መስተካከሉን እና በርካታ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውን ጠቅሰዋል፡፡   በመድረኩ አስተያየት የሰጡት የሲዳማ ክልል የመስኖ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መስፍን በላይ ከዚህ ቀደም ጥናቶች በሚገባ ሳይጠናቀቁ ወደ ግንባታ በመገባቱ ፕሮጀክቶች ይጓተቱ እንደነበር አስታውሰዋል። የስታንዳርድ መዘጋጀት የትኛው ተግባር መቅደም እንዳለበት በግልጽ ስለሚያስቀምጥ ይህንን ክፍተት ሙሉ በሙሉ እንደቀረፈው ገልጸዋል።   የኦሮሚያ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር አለሙ ረጋሳ በበኩላቸው አሰራሩ ሀገር በዘርፉ የያዘችውን ትልቅ የመስኖ ልማት እቅድ በጥሩ ሁኔታ ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።   የአፋር ክልል መስኖና ቆላማ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኢንጂነር መሐመድ ሁማድ አሁን ላይ ስታንዳርዱ በመዘጋጀቱና ስራዎች በህግና በስርዓት መመራት በመጀመራቸው፣ ቀደም ሲል በዘርፉ ይታይ የነበረውን ተግዳሮቶችን መድፈኑን ተናግረዋል።
ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው
Jun 22, 2026 234
ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና በአሪ ዞኖች የሚገኙ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ተናገሩ። ፋውንዴሽኑ ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ከመንግስታዊ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በወጣቶች የኢኮኖሚ አቅም ግንባታ ላይ ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክቷል።   በጂንካ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው ኤግዚቢሽን ላይ ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ስራ ፈጣሪ ወጣቶችም የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርጉላቸው ድጋፎች ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ገልጸዋል። በአሪ ዞን የደቡብ አሪ ወረዳ ነዋሪ ወጣት ያዕቆብ ገርሲኖ በፋውንዴሽኑ እና በመንግሥት ተቋማት ድጋፍ 10 አባላት ያሉት ማህበር በማቋቋም በንብ ማነብ ስራ እንደተሰማሩ ገልጿል። በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ በዶሮ እርባታ ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል ወጣት ወንድምነህ ሀብታሙ እንደገለፀው 10 አባላት ያለው ማህበር በማቋቋም በ45 ቀን ጫጩት አቅርቦት እና በዕንቁላል ጣይ ዶሮ እርባታ መሰማራታቸውን ጠቁሟል። ፋውንዴሽኑ እና መንግስታዊ ተቋማት ድጋፍ በዶሮ እርባታ በቂ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቁመው ፥ አሁን ላይ እስከ 4 ሺህ ጫጩቶችን ለገበያ በማቅረብ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ተናግሯል። ሌላው በደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ወጣት ሉቲየ ወንጌላ በበኩሉ 10 አባላት ያለው ማህበር በማቋቋም ፍየል በማሞከት ለገበያ የማቅረብ ስራ ላይ መሰማራታቸውን ገልጿል። በወሰዱት በቂ ስልጠናና እና ድጋፍ ፍየሎችን በማድለብና ለገበያ በማቅረብ የተሻለ ገቢ እያገኘ መሆኑንም ጠቁመዋል ።   የፋውንዴሽኑ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ሶስና ኃይለማርያም (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት የኃይለማርያም እና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማትና ከመንግስታዊ ተቋማት ጋር በመተባበር በደቡብ ኦሞ እና በአሪ ዞኖች በተመረጡ ወረዳዎች የወጣቶች የራስ ስራ ፈጠራ ፕሮጀክት ተግባራዊ እያደረገ ነው። የዚህ ፕሮጀክት ዓላማ ሥራ ፈላጊ ወጣቶችን በክህሎት ስልጠናዎች ማብቃት፣ ኢንተርፕራይዞችን እንዲያቋቁሙ መደገፍ፣ የፋይናንስ አቅርቦትን ማመቻቸት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የገበያ ትስስርና ተቋማዊ ድጋፍ እንዲኖር በማስቻል መንግስት ለወጣቶች የስራ ዕድል ለማመቻቸት እና የወጣቶችን የኢኮኖሚ አቅም ለማጎልበት እያደረገ ያለውን ጥረት ማገዝ እንደሆነ ገልጸዋል። ላለፉት ሁለት ዓመታት በየደረጃው ከሚገኙ መንግስታዊ መዋቅሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በሁለቱ ዞኖች 31 ሺህ 617 ወጣቶችን በንግድ ክህሎት ስልጠና በመስጠት የማብቃት ስራ መስራቱን አንስተዋል። የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ በበኩላቸው ፋውንዴሽኑን በዞኑ የሚገኙ ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን የክህሎት እና የፋይናንስ አቅም በማጎልበት ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሰፊ ርብርብ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ የፋውንዴሽኑ ድጋፍም ወጣቶቹ ውጤታማ እንዲሆኑ አቅምን ይፈጥራል ብለዋል። የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ጋያ በበኩላቸው ፋውንዴሽኑ በአርብቶ አደሩ አካባቢ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።   ፋውንዴሽኑ የወጣቶችን አቅም ከማጎልበት ባሻገር ተማሪዎችን የምገባ መርሃ ግብር በመደገፍ፣ ዘመናዊ እርሻን በማስተዋወቅ፣ በተፈጥሮ አያያዝና እንክብካቤ ረገድ ግንዛቤ በመፍጠር በጤናው ዘርፍ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ
Jun 22, 2026 390
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) የፌዴሬሽኑን አሰራርና መረጃ አያያዝ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመንና በጋራ ለመስራት የሚያስችል የፕሮጀክት ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ፌደሬሽኑ ዘመናዊ የምዝገባ ሥርዓትን በመዘርጋትና ተቋሙን ዲጂታላይዝ በማድረግ ረገድ ብዙ መሥራት እንደሚገባ አመልክተዋል። በስምምነቱ መሰረት በቴክኖሎጂ የዳበረ ተቋም ለመገንባት ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) በትብብር እንደሚሰራ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ፈጣንና ቀልጣፋ የአትሌቶች አገልግሎት ለመስጠት በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) የኢንፎርሜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃኒባል ለማ፤ አትሌቲክስ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ያኮራ ታላቅ ዘርፍ መሆኑን ገልጸዋል። የፌዴሬሽኑ የዲጂታል ሉዓላዊነት (Digital Sovereignty ) ለማጠናከር ፣ ከዓለም አትሌቲክስ ጋር ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖረው የሚያስችል የቴክኖሎጂ ትስስርን ጨምሮ አስፈላጊው ሁሉ ለማድረግ ተቋማቸው ለአትሌቲክሱ እድገት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ስምምነቱ ከስልጠና ማዕከላት ጀምሮ ፕሮጀክቶችን፣ ክለቦችን እና ተቋማትን ያቀፈ የአትሌቶች ምዝገባ ሥርዓትን የሚዘረጋ ሲሆን፤ የውድድሮችን የአደረጃጀትና የአመራር (ማኔጅመንት) ሥርዓት ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። ከአትሌቶች አገልግሎት ጋር የተያያዙ የኤምባሲ ጉዳዮችን ከእጅ-በእጅ (ማኑዋል) አሰራር ወደ ዲጂታል ሥርዓት የሚቀይር በመሆኑ፣ ይደርስ የነበረውን እንግልት እንደሚያስቀርም ፌዴሬሽኑ ገልጿል። በተጨማሪም ስምምነቱ የፋይናንስ፣ የንብረት አስተዳደር እና የግዥ ሥርዓቶችን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የሚያስችል ሲሆን፤ የፌዴሬሽኑን ድረ-ገጽ (ዌብሳይት) ማበልጸግን ጨምሮ በርካታ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎችን የሚያካትት ነው።
ዩኒቨርሲቲው የቱሪዝም ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ያጠናክራል
Jun 22, 2026 337
ሮቤ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝም ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን እንደሚያጠናክር ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው "የቱሪዝምና መስተንግዶ ትምህርትን በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ማዕቀፍ መቃኘት" በሚል መሪ ሐሳብ 2ኛውን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ኮንፈረንስ ማካሄድ ጀምሯል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እና የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፤ በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፉን በማልማት ዓለም አቀፍ ተመራጭነቷን ለማስፋት በምታደርገው ጥረት ቴክኖሎጂ ዋና ግብዓት ነው ብለዋል። በዚህም የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ከዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ጋር በማስተሳሰር ወደ ሥራ መገባቱንም አንስተዋል። ይህም በቱሪዝም ዘርፉ የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል ልማት በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የራሱ ድርሻ እንዳለው ጠቁመዋል። መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የባሌና አካባቢውን የቱሪዝም እምቅ አቅም ለማልማት የሚደረገውን ጥረት በምርምርና በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እንዲደገፍ ለማድረግ መሥራቱ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል። የአሁኑ የምርምር ኮንፈረንስ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ኢኒሼቲቭ ለማሳካት መሠረት እንደሚጥል ተናግረዋል። ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈው ይህ የምርምር መድረክ፤ ዩኒቨርሲቲው በቱሪዝም ዘርፍ የጀመረውን የማስተዋወቅ፤ የማነቃቃትና የምርምር ሥራዎች ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ተጨማሪ አቅም እንደሚሆንም አክለዋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን የቱሪዝም እምቅ አቅም ለማልማት የሚደረገውን ጥረት በምርምር እያገዘ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   ለዚህም በባሌና በምሥራቅ ባሌ አካባቢ የሚገኙ በርካታ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ የቱሪስት መስህቦችን በሳይንሳዊ መንገድ የማጥናት፤ የማስተዋወቅና እንዲለሙ በቅንጅት የመሥራት ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለአብነትም የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክና የድሬ ሼህ ሁሴን የመስህብ ስፍራዎች እንዲለሙና እንዲተዋወቁ ዩኒቨርሲቲው የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አመልክተዋል። ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀው ይህ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስም የቱሪስት መስህቦችን ለማልማትና ለማስተዋወቅ እያደረገ ላለው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፤ የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ በቱሪስት መዳረሻዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ብለዋል።   ለዚህም የሰው ኃይል ልማትን ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር ባለሙያዎች በዕውቀትና በክህሎት ብቁ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለተግባራዊነቱም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የቱሪዝምና የሆቴል ኢንዱስትሪውን የሚመጥን ብቁ ባለሙያ የማፍራት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፤ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ እያደረጋቸው ያሉ የምርምር ሥራዎች ለዚህ ጥረት ትልቅ አጋዥ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከኮንፈረንሱ መክፈቻ ጎን ለጎንም መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK) የመጡ የባለሙያዎች ቡድን ጋር በቅርብ ትብብር ያበለጸገውንና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀውን አዲሱን የዩኒቨርሲቲውን ድረ-ገጽ በይፋ አስመርቋል።
የሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም አስተማማኝ የሃይል አቅርቦት እንዲፈጠር እየተደረገ ነው
Jun 22, 2026 326
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦የሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም አስተማማኝ የሃይል አቅርቦት እንዲፈጠር እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ገለጹ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ለኢዜአ እንዳሉት፤ አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት መስመሮችንና የዲስትሪቡዩሽን ትራንስፎርመሮችን ብቃት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው። የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግርን ለመፍታት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማትን የማሻሻል፣ መልሶ የማቋቋምና የቅድመ-መከላከል ጥገና ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። ድንገተኛ ብልሽቶችን አስቀድሞ ለመለየትና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመዘርጋትም ዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ጥቅም ላይ እየዋሉ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ አገልግሎት፣ ከመንግሥትና የልማት አጋሮች የሚመነጭ የገንዘብ ሃብትን በመጠቀም መሰረተ ልማት የማሻሻል ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ከመሠረተ ልማት ግንባታው ጎን ለጎንም የደንበኞችን አገልግሎት ጥራትና ፍጥነት ማሻሻል የሚያስችሉ ሰፋፊ የትራንስፎርሜሽን ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን በመተግበር የኔትወርክ አቅምን የማሳደግ፣ መልሶ የማደራጀትና የቅድመ-መከላከል ጥገና ሥራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። ደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻልም የውስጥ አቅምን የማጠናከርና የጥገና ቡድኖችን በአዲስ መልክ የማደራጀት ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የተፈጠረው ውጤታማ የደንበኞች አገልግሎትም ውጤታማነትን እያሻሻለ መሆኑን አስረድተዋል።
ኢንስቲትዩቱ የፍትህ ዘርፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 20, 2026 1053
አዳማ፣ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ሕግ ምርምርና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የፍትህ ዘርፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ። ኢንስቲትዩቱ የፍትህ ሪፎርሙን ለማሳካት ያካሄዳቸውን የምርምር ውጤቶች በግብዓት ለማዳበር የሚያስችል የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አባገዳ አዳራሽ በማካሄድ ላይ ይገኛል።   የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት አቶ ገዛሊ አባ ሲመል ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት በጥናትና ምርምር የተደገፉ የመፍትሔ ሐሳቦችን እያቀረበ ይገኛል። በመድረኩ ላይ በቁልፍ የፍትህ ዘርፍ ጉዳዮች ዙሪያ የተከናወኑ አምስት የተለያዩ የምርምር ውጤቶች እንደሚቀርቡ ተናግረዋል። ምርምሮቹም የፍትህ አካላት ስነ-ምግባር፣ የፌዴራልና የክልል የህግ ተፈፃሚነት ወሰን ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶች፣ በፍትህ ዘርፉ የዲጂታል አገልግሎት ዘመን የቋሚና ተዘዋዋሪ ችሎት አስፈላጊነት፣ እንዲሁም የህግ ትርጓሜና የተፈፃሚነት ወሰን የተመለከቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህ የምርምር ውጤቶች ጠንካራ የፍትህ ስርዓት በመገንባት በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የፍትህ ዘርፍ ሪፎርም ለማሳካት ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተለይም በህግና በአሰራር ዙሪያ ያሉትን ክፍተቶች ለመድፈን በእጅጉ ያግዛሉ ብለዋል። የኦሮሚያ ህግ ምርምርና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ አዱኛ ሙሐመድ በበኩላቸው፤ ኢንስቲትዩቱ በክልሉ የፍትህ ስርዓትን ለማሻሻል እስካሁን ከ100 በላይ የምርምር ስራዎችን በማካሄድ በግብዓትነት እንዲያገለግሉ ማድረጉን ጠቁመዋል።   በተለይም በዘርፉ የተጀመሩ የሪፎርምና የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ስራዎችን ለማሳለጥ በጥናትና ምርምር ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ የፍትህ ስርዓቱን አሰራር ለማዘመንና በቴክኖሎጂ ለመምራት የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ለዛሬው መድረክ መቅረባቸውን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ ከጥናትና ምርምር ስራዎች ጎን ለጎን፣ ብቁ የፍትህ አካላትን ለማፍራትና ጥራትን ለማረጋገጥ ለህግ ባለሙያዎች የስልጠናና የአቅም ግንባታ ስራዎችን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝም ዋና ዳይሬክተሯ አክለዋል።   በመድረኩ ላይ በፌዴራልና በክልል የሕግ ወሰን ተፈጻሚነት ዙሪያ የተካሄደውን ምርምር ያቀረቡት አብዲሳ ጉርሜ (ዶ/ር)፤ የጥናቱ ውጤት በፌዴራልና በክልል የሕግ ተፈጻሚነት ረገድ የሚታዩ ውስንነቶችን በግልጽ በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከቱን አስገንዝበዋል። በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ከኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እና ከፌዴራል ፍትህ ኢንስቲትዩት የተጋበዙ ተመራማሪዎችና የህግ ምሁራን በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ስፖርት
ሜሲ የዓለም ዋንጫን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረ ወሰን በሰበረበት ጨዋታ አርጀንቲና ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች
Jun 22, 2026 445
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የምድብ 10 መርሐ ግብር አርጀንቲና ኦስትሪያን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በዳላስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሊዮኔል ሜሲ በ38ኛው እና በ95ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥሯል። ሜሲ በዓለም ዋንጫው ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 18 በማድረስ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን ክብረ ወሰን ከጀርመኑ ሚሮስላቭ ክሎዝ (16 ጎል) ተረክቧል። ሜሲ በስምንተኛው ደቂቃ ቡድኑ ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ስቷል። የ38 ዓመቱ ተጫዋች በአጠቃላይ ለሀገሩ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 122 በማድረስ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን አጠናክሯል። ውጤቱን ተከትሎ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ አርጀንቲና በስድስት ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፍ ገብታለች። ኦስትሪያ በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዚሁ ምድብ ጆርዳን ከአልጄሪያ በሳንፍራንሲስኮ ቤይ ኤሪያ ስታዲየም ከማለዳው 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሁለቱ ሀገራት በመጀመሪያ ጨዋታቸው ሽንፈት አስተናግደዋል።
ሀዲያ ሆሳዕና ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
Jun 22, 2026 330
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሀዲያ ሆሳዕና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብሩክ በየነ በመጀመሪያ አጋማሽ ማብቂያ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሀዲያ ሆሳዕና በ46 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 13ኛ ከፍ ብሏል። በሊጉም 11ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 12ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ42 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ባለፉት አራት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ዛሬ አስቀድመው በተደረጉ የ36ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ፋሲል ከነማ አርባምንጭ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ አርባምንጭ ከተማ ከሊጉ የወረደ የመጀመሪያ ቡድን ሆኗል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 ረቷል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የ36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተጠናቋል።
አርባምንጭ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ወረደ
Jun 22, 2026 250
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፋሲል ከነማ አርባምንጭ ከተማን 2 ለ 0 ረትቷል። ታምራት እያሱ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ በሊጉ 15ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርባምንጭ ከተማ በ35 ነጥብ ሁለት ጨዋታዎች እየቀሩት የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዞ ከፕሪሚየር ሊጉ መውረዱ የተረጋገጠ የመጀመሪያው ክለብ ሆኗል። በዘንድሮው የውድድር ዓመት አራት ክለቦች ከሊጉ ይወርዳሉ። ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ፋሲል ከነማ በበኩሉ በ52 ነጥብ ደረጃውን ከስድስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉም 13ኛ ድሉን አስመዝግቧል። የፋሲል ከነማው ታምራት እያሱ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 14 ከፍ በማድረግ ተመሳሳይ ግብ ካላቸው የሲዳማ ቡናው አቤል ያለው እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ ናትናኤል ዳንኤል ጋር በጋራ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል። በሌላኛው መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በረከት ወልደዮሐንስ እና አቤል ሀብታሙ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ያሬድ ዳርዛ ለወላይታ ድቻ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከአራት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ50 ነጥብ ከነበረበት ስምንተኛ ደረጃ ወደ አምስተኛ ከፍ ብሏል። በውድድር ዓመቱ 12ኛ ድሉን አግኝቷል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ዘጠነኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወላይታ ድቻ በ47 ነጥብ ከነበረበት 7ኛ ደረጃ ወደ 8ኛ ዝቅ ብሏል።
የዓለም ዋንጫ ሁለተኛ ዙር ጨዋታ፤ ሴኔጋል ከኖርዌይ፡አልጄሪያ ከጆርዳን
Jun 22, 2026 357
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ 9 እና 10 ሁለተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ። በምድብ ዘጠኝ ኖርዌይ ከሴኔጋል በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ኖርዌይ ኢራቅን 3 ለ 1 ስትረታ ሴኔጋል በፈረንሳይ 3 ለ 1 ተሸንፋለች። ኖርዌይ ካሸነፈች ጥሎ ማለፍ መግባቷን ታረጋግጣለች። የምዕራብ አፍሪካዋ ሴኔጋል ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ህልሟን እውን ለማድረግ ከጨዋታው ሶስት ነጥብ ማግኘት ይጠበቅባታል። በዚሁ ምድብ ፈረንሳይ ከኢራቅ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ላይ በፊላደልፊያ ስታዲየም ይጫወታሉ። የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት ያገኘችው ፈረንሳይ ድል ከቀናት ወደ ጥሎ ማለፉ ትገባለች። ኢራቅ በውድድሩ ላይ ለመቆየት ከጠንካራዋ ፈረንሳይ ሶስት ነጥብ ማግኘት ይጠበቅባታል። በምድብ 10 ጆርዳን ከአልጄሪያ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ በሳንፍራንሲስኮ ቤይ ኤሪያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታቸው ጆርዳን በኦስትሪያ 3 ለ 1፣ አልጄሪያ በአርጀንቲና የ3 ለ 0 ሽንፈት አስተናግደዋል። ሁለቱ ቡድኖች የመጀመሪያ ድላቸውን ለማስመዝገብ ይፋለማሉ። አሸናፊው ቡድን ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት ተስፋውን ያለመልማል። በዚሁ ምድብ አርጀንቲና ከኦስትሪያ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በዳላስ ስታዲየም ይጫወታሉ። የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸውን ያሸነፉት ሁለት ሀገራት የሚያደርጉት ጨዋታ ትኩረትን ስቧል። ጨዋታውን የሚያሸንፈው ሀገር ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ያረጋግጣል።
አካባቢ ጥበቃ
ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቀነስ የሚያስችሉ የጋራ ተጨባጭ መፍትሔዎችን መተግበር ይገባል
Jun 22, 2026 509
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን መቀነስ የሚያስችሉ የጋራ ተጨባጭ መፍትሔዎችን መተግበር እንደሚገባ የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዝደንት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንት ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል። የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዝደንት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በሳምንቱ እየተሳተፉ ነው። በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በሰኔ ወር በለንደን ታይቶ የማይታወቅ የሙቀት መጠን ሊኖር እንደሚችል መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ጠቅሰዋል። ይህም የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መከላከል እንደሚያስፈልግ ሁነኛ ትምህርት የሚያስተላልፍ መሆኑን ገልጸዋል። እየተስተዋለ ያለው ከፍተኛ የሙቀት መጠን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጨባጭ የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት መርሃ ግብር ቀርጾ መተገበር የግድ መሆኑን ያስገነዘበ ነው ብለዋል። በለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንትም ለዓለም የሚበጁ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ መፍትሔዎችን ማፍለቅ ከሁሉም የሚጠበቅ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። የለንደን የአየር ንብረት ለውጥ የድርጊት ሳምንት እስከ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።  
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የዘላቂ ልማት ግቦች በተግባር እየተተረጎሙ መሆናቸውን የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው
Jun 22, 2026 417
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የዘላቂ ልማት ግቦች በተግባር እየተተረጎሙ መሆናቸውን የሚያሳይ ህያው ምስክር መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና የተቋማት ክትትል ሚኒስትር ዲኤታ አክሊሉ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አመራርና ሠራተኞች ጋር በመሆን በየካ ተራራ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል።   በዚሁ ወቅት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና የተቋማት ክትትል ሚኒስትር ዲኤታ አክሊሉ ታደሰ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የዘላቂ ልማት ግቦች በተግባር እየተተረጎሙ መሆናቸውን የሚያሳይ ህያው ምስክርና ቁልፍ ማሳያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ሰፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸው፤ በተደረገው አገራዊ ርብርብ 48 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውንና ዘንድሮም 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ መያዙን አስታውቀዋል። ዓለም በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በርካታ ጉዳቶችን እያስተናገደች ባለችበት በአሁኑ ወቅት፣ ዘላቂ ዕድገትን ማረጋገጥ የሚቻለው ተፈጥሮን በመጠበቅና በመንከባከብ መሆኑን ጠቁመዋል።   ኢትዮጵያ እያከናወነችው ባለው በዚህ መርሃ ግብር በረሃማነትና የአየር ንብረት መዛባት በጉልህ እየቀነሰ መምጣቱንም ተናግረዋል። የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል አካሉ ካሳ በበኩላቸው በዚሁ ስፍራ ችግኞችን መትከላቸውን ገልጸው፤ አካባቢው ቀድሞ ከነበረበት መራቆት በጉልህ መለወጡን መስክረዋል። የአረንጓዴ አሻራ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መርሃ ግብር መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰራዊቱ ሀገር ከመጠበቅ ጎን ለጎን በዚህ አገራዊ ጥሪ ላይ አሻራውን እያሳረፈ እንደሚገኝና መርሃ ግብሩም ሰራዊቱ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠብቀው መሆኑን አስገንዝበዋል። ከቤተ መንግሥት አስተዳደር የመጣው ሀብታሙ ዮናስ በበኩሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአመት ዓመት በተሳትፎም ሆነ በሚተከሉ ችግኞች ቁጥር እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ ዘንድሮ የተያዘው አገራዊ ዕቅድ ግቡን እንዲመታ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጠይቋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፈችው ምናለሸዋ ማንደፍሮም የአረንጓዴ አሻራ ለትውልድ የተሻለች ሀገር የምናስተላልፍበት በመሆኑ ሁላችንም አሻራችንን ማኖር አለብን ብላለች፡፡ በተመሳሳይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፈው ተመስገን በለጠ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ትልልቅ ውጤቶችን እያስገኘ መሆኑን ገልጾ የነገዋን ኢትዮጵያ የተሻለች ለማድረግ ሁሉም በጉልህ መሳተፍ እንዳለበት አሳስቧል።
አረንጓዴ ዐሻራ ለኢትዮጵያ ታላቅ ክብር እና ተሰሚነት አጎናጽፏታል- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 22, 2026 489
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ አረንጓዴ ዐሻራ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ረገድ ለኢትዮጵያ ታላቅ ክብር እና ተሰሚነት ማጎናጸፉን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ አረንጓዴ ዐሻራ በተባበሩ ክንዶችና በመደመር የከበረ እሳቤ የመስራት ምስክር ነው ብለዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሠራተኞች ጋር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጫካ ፕሮጀክት ዛሬ መካሄዱንም ጠቁመዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ እንደ ሀገር የውበት ምንጭ የኢኮኖሚ ተደማሪ አቅም ይሆናል ተብሎ ታቅዶ የተሠራና በውጤት ፍሬ አፍርቶ እየታየ ያለ ተግባር መሆኑን አመልክተዋል።   ይህ በተግባር የተደገፈ ግዙፍ የአረንጓዴ ልማት ጉዞ፣ ከኢኮኖሚያዊና የአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው አልፎ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ረገድ ለሀገሪቷ ታላቅ ክብር እና ተሰሚነት አጎናጽፏታል ነው ያሉት። የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ በመሳብ ላይ የሚገኘው ይህ ስኬት፣ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) በኩራት ለምታስተናግደው ታሪካዊ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ጠንካራና አስተማማኝ መሰረት መጣሉን ተናግረዋል።   ይህ ሁለንተናዊ እመርታ የመንግሥትንና የዜጎችን ትጋት የሚያሳይ፣ መላው ኢትዮጵያውያንን እጅግ ሊያኮራ የሚገባ ታላቅ ሀገራዊ ድል ነው ብለዋል። በዚህ ዓመት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ያቀድነውን ግብ ለማሳካት በኅብረት እንትከል፣ እንንከባከብ ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ የኢትዮጵያን ስምና ዝና በዓለም አደባባይ ከፍ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 22, 2026 289
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የግብርና ምርታማነትን በማሳደግና በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ስምና ዝና በዓለም አደባባይ ከፍ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አመራርና ሠራተኞች ጋር በየካ ተራራ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢ ባህል እየሆነ መጥቷል ብለዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የግብርና ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ስምና ዝና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ በማድረግ ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተግባራዊ ስራ እያከናወነች የምትገኝ ሀገር መሆኗን ለዓለም በማሳየት ተሰሚነቷንና ተደማጭነቷን ያጎለበተ ብሔራዊ የልማት ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።   የውሃ ሃብት አቅምን በማሳደግና ከገፀ ምድር የነጠፉ ሐይቆች መልሰው እንዲያንሰራሩና የውሃ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን አስረድተዋል። በደን ሃብት መመናመን ሳቢያ የሚፈጠርን የአፈር መሸርሸር በማስቀረትም ከፍተኛ ጠቀሜታ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። በሌማት ትሩፋት የፍራፍሬ ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራና በሁሉም የግብርና ዘርፎች ምርታማነትን በማሻሻል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አብራርተዋል። የዝናብ መጠንን በማሻሻልም ክረምት ከበጋ ለግብርና ሥራ መሳለጥ አይነተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።   ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኝ መትከሏን በማንሳት፥ ዘንድሮም ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ሀሳብ 8 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል በበቂ ዝግጅት ወደ ሥራ መገባቱን አንስተዋል። የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በተያዘው ዕቅድ መሠረት ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 10952
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 8124
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 6942
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 6843
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Jun 21, 2026 743
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 14/2018 (ኢዜአ) ፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? በሳምንቱ ቢሾፍቱ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከባሕር ጠለል በላይ በ1 ሺህ 910 ሜትር ከፍታ ላይ በምትገኘው ቢሾፍቱ ግንባታው በመከናወን ላይ ይገኛል። የኤርፖርቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ግዙፍ የልማት ፕሮጀክት ነው።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የቢሾፍቱ ኢርፖርት ኢትዮጵያን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ማዕከላት ተርታ ለማሰለፍ የሚያስችል ታሪካዊ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ሳምንት ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በስፍራው በመገኘት የግንባታውን ሂደት የተመለከቱ ሲሆን ግንባታውን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅም ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ጥረት እየተገነባ ይገኛል ብለዋል። በእለቱም የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በቢሾፍቱ ያስጀመሩ ሲሆን ‎ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞች የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጎሮ ወረዳ በመገኘት የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያስጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክትም ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው! ስለሆነም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በዚህ ሥራ እንዲሳተፍ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል። የሀገር መከታና የህዝብ አለኝታ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የህዝብ ወገንተኝነቱንና እና አለኝታነቱን በተግባር ማሳየቱን ቀጥሎበታል። ሰራዊቱ በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ ህዝባዊ ሰራዊት መሆኑን አሳይቷል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ተላላቅ መርሃ ግብሮች ባከበረበት ወቅት በሰሜን ጎንደር ዞን የ"ጭና ሰማዕታት መታሰቢያ ጤና ጣቢያ" ገንብቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ አስረክቧል።   በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰራዊቱ የጀግንነት ታሪክ እንደ ውቅያኖስ የማይነጥፍ ከመሆኑም በላይ፣ በጭና ግንባር የተቀዳጀው ድል የጠላትን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅም ሙሉ በሙሉ የሰበረ የድል ማህተም ነው ብለዋል። ለልማት- የሃይል አማራጭን ማስፋት በኢትዮጵያ ከከተማ እስከ ገጠር የተሰናሰለ የሃይል ልማትን በማስፋት አማራጭ የሃይል አቅርቦት ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዚህ ሳምንትም በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ ከ312 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችል የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ለመገንባት መሰረተ ድንጋይ ተቀምጧል።   የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሡልጣን ወሊ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጥረት በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ለዘላቂ ልማትና ለዜጎች ተጠቃሚነት የሃይል አማራጭን የማስፋት ስራ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አንስተዋል። በምርታማነት የምግብ ስርዓት ችግርን መፍታት በኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ችግርን ለመፍታት እስከ ታችኛው መንግስታዊ መዋቅር ድረስ የሚዘልቁ የተለያዩ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በዚሁ መሰረትም በምግብ ስርዓት አለመስተካከል የሚከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገልጿል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት በክልሉ ስርዓት ምግብ ሽግግርና የቀዳማዊ ልጅነት ልማት ፍኖተ ካርታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ችግር ፈች ምርምር ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በምርምር ሥራዎችና በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጸውም በዚህ ሳምንት ነው። በዩኒቨርሲቲው በምርምር ፕሮጀክቶች እና በማህበረሰብ አገልግሎቶች የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምግምና ቅንጅታዊ ሥራን ለማጠናከር ያለመ መድረክም አካሄዶ ነበር። መድረኩ በተለይ ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ዕድሎችን አስፍቶ ለመጠቀም የተመራማሪዎችን አቅም ማሳደግ ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ ከ84 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ 54 የምርምር ሥራዎችን እንዲሁም 70 የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። በቀብሪ በያህ ከተማ የወጣቶች የልማት ተጠቃሚነት በሶማሌ ክልል የልማትና የምርታማነት አጀንዳዎች በውጤታማነት ቀጥለዋል። የወጣችንና አጠቃላይ የክልሉን ህዝብ የልማት ፍላጎት መሰረት አድርገው እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው። በዚሁ መሰረት በክልሉ ፋፈን ዞን ቀብሪ በያህ ከተማ በማህበር ተደራጅተው ሥራ የፈጠሩ ወጣቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። አብዲከሪን መሀመድ እና ጓደኞቹ በማህበር ተደራጅተው በዶሮ እርባታ በመሰማራት በሌማት ትሩፋት የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። ሥራውን ከጀመሩ ወዲህ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ ለሌሎች ወገኖችም ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙ ይናገራሉ። እንደ አጠቃላይ በሶማሌ ክልል ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ቀጥለዋል። የበጀት ክለሳ በዚሁ ሳምንት የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የ2018 የበጀት ዓመት የ11 ወራት እቅድ አፈጻጸም መነሻ በማድረግ የቀረበለት የበጀት ክለሳ አፅድቋል። ካቢኔው በክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አማካኝነት የቀረበለትን ከ301 ሚሊየን 693 ሺህ 178 ብር የበጀት ክለሳ ነው ተወያይቶ ያፀደቀው። የበጀት ክለሳው በተለይም የፊስካልና ፋይናንሻል አፈፃፀማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ፕሮጀክቶችን በመለየት የላቀ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ላላቸውና የበጀት እጥረት ላጋጠማቸው ጉዳዮች የሚውል ነው ተብሏል። የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮቿን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት ልትሰጠው እየተጋች ነው። ለዚህ ዋና ማሳያው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ነው። ማዕከሉ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን የተገነባውን ኮንታ መሶብ የአንድ ማዕከል መርቀው በይፋ አገልግሎት አስጀምረዋል።   መሶብ የአንድ ማዕከል በተበታተነ ሁኔታ ይሰጡ የነበሩ የመንግሥትና የማኅበራዊ አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር በማሰባሰብ ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው። የኮንታ ማዕከልም ሕዝቡ ከቢሮ ወደ ቢሮ በመዘዋወር የሚያጠፋውን ጊዜ፣ ወጪና እንግልት በእጅጉ በመቀነስ ጥራት ያለው፣ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት እንዲያገኙ ያግዛቸዋል ተብሏል።   የስደተኞች መጠጊያ- ኢትዮጵያ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞች መጠጊያ የሆነችው ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የስደተኞች ቀን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ተከብሯል። የክልሉ ‎ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ክልሉ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞችን ከመቀበል ባለፈ ስደተኞችን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።   በክልሉ አራት መጠለያ ጣቢያዎች ላይ ከ112 ሺህ በላይ ስደተኞች እንደሚገኙ ገልፀው፥ ስደተኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ጠንካራ መስተጋብር በመፍጠር በአብሮነት እየኖሩ ነው ብለዋል። ስደተኞች የውሃ፣ የትምህርት የጤናና ሌሎች የመሠረተ ልማቶችን ከተቀባዩ ማህበረሰብ እኩል ተጠቃሚ መሆናቸው የኢትዮጵያን ስደተኞች አያያዝ የተሻለ ተሞክሮ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ጋምቤላ የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አባላት በመጪው የህዝብ ውክልና ስራ ስምሪት ወቅት የሚያከናውኗቸውን ተግባራት በተመለከተ የኦሬንቴሽን ፕሮግራም አካሂዷል። የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ጁል ናንጋል፣ የህዝብ ውክልና ተግባር የምክር ቤት አባላት ዋና ሃላፊነት መሆኑን ገልፀው፣ አባላቱ ወደ ህዝቡ በመቅረብ የህብረተሰቡን ፍላጎት፣ ችግርና አስተያየት በአግባቡ በማሰባሰብ ለመንግስት አካላት ማድረስ እንደሚገባቸው ተናግረዋል።   ምክትል አፈ ጉባኤው እንዳሉት፣ የህዝብ ውክልና ስራ በዜጎችና በምክር ቤቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና የህዝብ ተሳትፎን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ያለው በመሆኑ አባላቱ በተሰጣቸው ኃላፊነት ትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። ድሬደዋ ድሬደዋ የመስኖ ግንባታ። 'በቆላማ አከባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም' በሁላሁሉል ገጠር ቀበሌ ውስጥ የከርሰ ምድር ውሃን በመጠቀም የተሰሩ የንፁህ መጠጥ ውሃና የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች፥ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) በተገኙበት ተመርቋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) እና የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ ግድቡን በመረቁበት ወቅት ከምንም በላይ ለሰው ልጆች ህይወት እጅግ አስፈላጊ የሆነውና፥ የአስተዳደራችን የገጠር ነዋሪ ህብረተሰብ መሠረታዊ ፍላጎትና የረጅም ዘመናት ምኞት የነበረውን፥ የውሃ ጥያቄ በጋራ ርብርብ መመለስ መቻል የሚሰጠው ደስታ እጅግ ልዩ ነው ብለዋል ከንቲባው።   የድሬዳዋን ማህበረሰብ የምግብ ሉኣላዊነት የማረጋገጥ፣ አርሶአደሩ ነዋሪ ከራሱ አልፎ ለገበያ በማቅረብ ኑሮውን እንዲያሻሽል እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመስኖ ልማት ሥራዎችን እንዲያከናውን በማገዝ ረገድ ቀጣይነት ያለው ስራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። አፋር ሳምንቱ በአፋር ክልል በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ያሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ወጣቶች፣ ባህልና ስፖርት ቢሮ ያስታወቀበትም ነበር። የአፋር ክልል አብዛኛው ማህበረሰብ ከፊል አርብቶ አደርና አርብቶ አደር በመሆኑ፣ በየዓመቱ የሚከናወኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክፍተቶች ለመሙላት ትልቅ ሚና አላቸው። በተለይም የአየር ንብረት መለዋወጥ፣ የውሃ እጥረት እና አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎችን ተቋቁሞ ዘላቂ ልማት ለማምጣት የወጣቶችና የህብረተሰቡ የተቀናጀ አቅም ወሳኝ ግብዓት ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። ማጠቃለያ ሳምንቱ በሁሉም ክልሎች መደበኛ የልማት፣ የማህበራዊ እና የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው የቀጠሉበትም ነበር። በሁሉም ክልሎች የስድስተኛ እና ስምንተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተካሄዷል። በተመሳሳይ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ዝግጅት በሁሉም ክልሎች እየተከናወነ ይገኛል።  
 የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jun 15, 2026 2634
በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉የተራሮች ስር ፈርጥ - ወልዲያ የዛሬው የወፍ በረር ምልከታችን የሚጀምረው የተራሮች ስር ፈርጥ በሆነችው ወልዲያ ከተማ በመገኘት ነው። ከደሴ በ120 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውና በረጃጅም ተራሮች የተከበበችው ወልዲያ ከተማ ከነበረችበት ጉስቁልና ወጥታ አሁን ላይ በውበት ፈክታ ትገኛለች። በሳምንቱ በዚህች ከተማ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኮሪደር ልማቷንና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፤ ተዘዋውረውም ጎብኝተዋል። በተለያዩ ታሪካዊና ባህላዊ ትውፊቶች ስሟ ጎልቶ የሚጠራው ወልዲያ እንደ ከዋክብት ፈክታ እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር እየተስፋፉ መሆኑን አንስተው በቀጣይ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ትገሰግሳለች ብለዋል። 👉የሸደር አዳሪ ትምህርት ቤት የሚቀጥለው መዳረሻችን በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን አውበሬ ወረዳ ሼደር ከተማ አዲስ የተገነባውን አዳሪ ትምህርት ቤት መመረቅ ይሆኗል። የትምህርት ቤቱን ግንባታ መርቀው ስራ ያስጀመሩት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ናቸው። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው፤ በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋት የተማረ ትውልድ ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በ138 ሚሊየን ብር የተገነባው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ስራ መጀመሩ ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል። 👉የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የበረራ ቅኝታችን ቀጥሎ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በመስኖ እየለማ ያለ የስንዴ ምርት የመጎብኘት እድል አግኝተናል። በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል መሰብሰብ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። የግብርና ሜካናይዜሽንን በስፋት በመጠቀም እንዲሁም ፈጠራን በማከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ጥረቱ በተሳካ መልኩ መቀጠሉን አንስተዋል። 👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ዓለም አቀፍ ክስተት ነው። ችግሩ በተለይም በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ ይገኛል። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መጠን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ መፍትሄ ለመስጠት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። በዚህ ረገድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት በሚከናወኑ ሥራዎች በምርምር እያገዙ ናቸው። በሂደቱ ውጤታማነት ላይ የሚመክር መድረክ በሰመራ በተደረገበት ወቅት የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ችግሩን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት በምርምርና በማማከር እያገዙ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሰዎች ህገወጥ ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ለህብረተሰቡ እየሰጡ ናቸው። 👉የኢትዮጵያ እያመረተች ነው በአማራ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እና ሌሎችም በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለውጭ ምንዛሬ አይነተኛ የገቢ ምንጭ መሆን አስችሏል ብለዋል። 👉መሶብ በአርባ ምንጭ፣ ዲላ እና ነቀምቴ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት በዚህ ሳምንት አርባ ምንጭ፣ እና ዲላ ከተሞች ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። የመሶብ ማእከላቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል። የዲጅታል አሰራርን በማስፋት ለዜጎች ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። 👉ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩ ስለመሆኑ ያነሳል። በመሆኑም ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን አደራጅቷል። በመሆኑም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በእለቱ ድምፅ መስጠት ካልቻሉት መካከል የሰሜን ምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በፊት ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፃቸውን ሰጥተዋል። በተመሳሳይ በአፋር ክልል እና በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያዎች የሚገኙ ዜጎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል። 👉የመኸር እርሻ ንቅናቄ በሲዳማ ክልል የመኸር እርሻን በንቅናቄ በመምራት የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡና ገበያን የሚያረጋጉ የግብርና ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በንቅናቄ መድረኩ ርእሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት መሬት ጦሙን እንዳያድርና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ እንዲሁም ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠት ምርታማነቱን ማሳካት አስችሏል። ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል የበልግ ሰብልን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። ይህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ በማምረት ገበያን ለማረጋጋትና ለኢንደስትሪዎች ግብአት ለማቅረብ ያስችላል ነው የተባለው። በምርት ዘመኑ የተያዘውን እቅድ ለማሳካትም አመራሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር ለውጤቱ መትጋት እንዳለበትም በውይይቱ ተነስቷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምርጥ ዘር ብዜትን በዓይነት፣ በመጠንና በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ ተችሏል። ቢሮው በግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ እና በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዘር ብዜት ዕቅድ አፈጻጸምና ዝግጅት ላይ ያተኮረ የባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ እንደገለጹት፤ በክልሉ የምርጥ ዘርን በጥራትና በመጠን ለአርሶ አደሩ በወቅቱ በማድረስ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል። ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ለኢንዱስትሪዎች በቂ ግብዓትን ለማቅረብና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር አግዟል። ተግባሩን በማስቀጠልም በ2017/18 የምርት ዘመን በክልሉ ከ2 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ30 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ማምረት መቻሉንም ገልጸዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት
Jun 14, 2026 1997
በኢዜአ ዐይን …! በሙሴ መለሰ አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው።በዚህ ሂደት ደግሞ የኢትዮጵያ ድንቅ ስራ የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊትአውራሪነት ይጠቀሳል። መርሐ-ግብሩ የጋራ ነው በሚል ዕሳቤ በርካቶችን በንቃት አሳትፎ ለዓለም የሚደርስ የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ዐሳይቷል። የደን ሽፋን መጠንን አሳድጓል። ይህም በዓየር ንብረት ለውጥ ላይ የራሱን ሚና እያበረከተ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአረንጓዴ ዐሻራ ሚና ልቆ ይነሳል። ይህም የተራቆተ መሬትን ወደ ነበረበት ከመመለስ፣ የውኃ ሀብት አሥተዳደርን ምቹ ከማድረግ እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ጋር የሚያያዝ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብሩ በዕድሜ፣ በጾታ፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሥራ ዘርፎች፣ በኑሮ ደረጃ፣ በሐይማኖት ሳትለይ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች እንዲሳተፉበት በማድረጓ በዘርፉ ስኬታማ ጉዞ ላይ ናት። ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀት ከመሆን አልፎ ለጎረቤቶቿ ችግኝ በመለገስ መርሐ-ግብሩ እንዲስፋፋ እየተጋችም ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ሲናገሩ፤ አረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያ ትላልቅ ነገር አስባ፣ ትላልቅ ነገር ተልማ፣ ትላልቅ ነገር አቅዳ እና ሕዝቦቿን አስተባብራ ማሳካት እንደምትችል ለሌሎቹ ማሳያ ነው ማለታቸውም ከላይ ያነሳነውን ሐሳብ ያዳብረዋል። በተጨማሪም አረንጓዴ ዐሻራ በልዩ ትኩረት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሳይቆራረጥ እየተሠራ መሆኑን፤ በየዓመቱም በሚተከሉ ችግኞች ብዛት፣ በሚተከልበት መሬት ስፋት እና በሚሳተፉ ታታሪዎች ቁጥር እያደገ መሆኑን ያመላክታል። በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች እየወጡ በችግኝ ተከላ መሳተፋቸው የሀገርን የጋራ ራዕይ ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 7002
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ትንታኔዎች
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 2951
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ።   ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…! 
Jun 15, 2026 1723
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 7002
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው?
Jun 12, 2026 2700
የጤና ነገር … በዮሐንስ ደርበው የሰው ልጅ ሊሻሻሉ በሚችሉ እና በማይችሉ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ለልብ ህመም ሊጋለጥ እንደሚችል የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የአዋቂ የልብ ሕክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ብርሃኑ ሞገስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የልብ ህመም ከተወሳሰብ ዘላቂ የጤና እክል እስከ ድንገተኛ ኅልፈት ያደርሳል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ሰዎች ማሻሻል በሚችሏቸው (ሞዲፋይብል) እና ማሻሻል በማይችሏቸው (ነን ሞዲፋይብል ወይም ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች) ለልብ ህመም ሊጋለጡ እንደሚችሉ ዶክተር ብርሃኑ ይገልጻሉ። መሻሻል ከሚችሉ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል፤ ከፍተኛ ጭንቀት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ ከፍተኛ የደም ግፊት ህመም (በአግባቡ መድኃኒቱ ካልተወሰደ)፣ተገቢ ያልሆነ የስብ ክምችት፣ ከፍተኛ ውፍረት (ክብደት)፣ በቂ እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ጤናማ አመጋገብ አለመኖር እንዲሁም አብዝቶ ስኳር፣ ጣፋጭና አልኮል መጠቀም የሚሉትን ይጠቅሳሉ፡፡ እንዲሁም ሰዎች ማሻሻል ከማይችሏቸው (ተፈጥሯዊ) አጋላጮች መካከል፤ በቤተሰብ የሚተላለፍ መኖሩን፣ በዕድሜ መጨመር የሚከሰት መሆኑን (ለምሳሌ፡- ወንድ ከ45 ሴት ከ55 ዓመት በላይ ሲሆናቸው ለልብ ህመም ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩን) እንዲሁም ወንዶ ከሴቶች በይበልጥ ለልብ ህመም ተጋላጭ የመሆናቸው አጋጣሚ ሰፊ ሊሆን እንደሚችልም አብራርተዋል፡፡ በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የልብ ህመም ምልክቶች የደረት ውጋት በግራ በኩል ወይም መሐል ላይ፣ ከወትሮው የተለየ ድካም፣ ትንፋሽ ማጠር፣ ከመደበኛው የተለየ የልብ ምት መኖር፣ የሰውነት በተለይም እግር አካባቢ እብጠት፣ ራስን መሳት እና ሳል የልብና ተያያዥ ህመም ምልክት ሊሆኑ እንደሚችሉ አብራርተዋል። የልብን ጤናን ለመጠበቅ በተቻለ መጠን ጤናማ አመጋገብን መከተል እንደሚገባ የሚመክሩት ዶክተር ብርሃኑ፤ አትክልት ማዘውተር፣ ምግብ ሲዘጋጅም ፈሳሽ ዘይት መጠቀም፣ ስኳር፣ ጨው እና ጣፋጭ ነገሮችን መገደብ ከተቻለም ማስወገድ እንደሚገባ ይመክራሉ፡፡ አካላዊ እንቅስቃሴ ማዘውተር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ይህም ብስክሌት መንዳት፣ በእግር እንቅስቃሴ ማድረግ፣ ዋና መዋኘት፣ እስከሚያልብ እና የልብ ምት እስከሚጨምር ብሎም እስከሚደክሙ የአካል ብቃት መሥራት የልብን ጤና ለመጠበቅ አስተዋጽዖ አለው ነው ያሉት፡፡ ጤናማ የሰውነት ክብደት እንዲኖር ማድረግ ተገቢ መሆኑን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ “ቦዲ ማስ ኢንዴክስ (ቢ ኤም አይ)” ከ18 ነጥብ 5 እስከ 25 እንዲሆን ይመከራል ብለዋል፡፡ ሲጋራ አለማጨስ፣ አልኮል አለመጠቀም፣ የስኳር ህመምና ከፍተኛ ደም ግፊት ካለም የመድኃኒት አወሳሰድን አለማስተጓጎል፣ አመጋገብ ላይ ስብ አለማብዛትና አብዝቶ አለመቀመጥ የልብ ህመምን ለመከላከል እንደሚያግዙ ነው ያስረዱት፡፡ ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በታች የሆኑ ጤናማ ሰዎች ከአንድ እስከ ሦስት ዓመት ባሉ ጊዜያት አንድ ጊዜ፣ ዕድሜያቸው ከ45 በላይ የሆኑ በየዓመቱ እንዲሁም የልብ ህመም ያለባቸው እንደሁኔታው በየጊዜው ክትትል እንዲያደርጉም መክረዋል፡፡ ሰዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እራሳቸውን ከልብ ህመም እንዲጠብቁ መክረው፤ ከዚህ ያለፈ ችግር ሲኖር ቶሎ የሕክምና ክትትል ማድረግ እና “ዛሬ ነገ” በማለት ጊዜ እያባከኑ ህመሙ ውስብስብ ደረጃ እስኪደርስ መጠበቅ እንደማይገባቸው አሳስበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ጤና #የልብ_ህመም
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 2165
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 16361
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 9439
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 15200
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 86336
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 67886
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 48207
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 45772
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 34484
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 33977
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 33435
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 32674
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 86336
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 67886
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 48207
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 45772
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም
Jun 5, 2026 12779
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰርን ለመከላከል ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች በወቅቱ ካልታከመ ለኩላሊት መድከም፣ ለደም መመረዝና ለሞት የሚያደርሰው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 8244
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም