ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
21ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ ይከበራል-አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር
Sep 1, 2026 63
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2018 (ኢዜአ)፦21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሕዝቦችን ትስስርና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ እንደሚከበር የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። የ21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ በበዓሉ መሪ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ እያካሔደ ይገኛል። በውይይት መድረኩ የሁሉም ክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች አፈ-ጉባዔዎች፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች፣ሚኒስትሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የዘንድሮው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ኢትዮጵያ ያካሔደችው ስኬታማ ሀገራዊ ምርጫ እና ሀገራዊ ምክክር በውጤታማነት በተጠናቀቀበት ማግሥት መሆኑ ከወትሮው ለየት ያደርገዋል። በዓሉ በሕዝቦች መካከል የሚደረጉ ባሕላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልውውጦችን በማስፋት ዘላቂ መከባበርና አብሮነትን ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የበዓሉ ዝግጅት በየደረጃው ከሚገኙ ማኅበረሰቦች ጋር በመቀናጀት ሕዝባዊ መሠረቱን የጠበቀና ሕብረ-ብሔራዊ ውበቱን በሚገልጽ መልኩ እንዲከበር አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። 21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሕዝቦችን ትስስርና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ እንደሚከበር ጠቅሰው፤ ለዚህም ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዓሉ በክልሎች፣በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በፌዴራል ተቋማት፣ ከሀገር ውጭ በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ሲከበር ቆይቶ ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ማጠቃለያው ይሆናል።
በአማራ ክልል የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ አበረታች ውጤት እያስመዘገበ ነው
Sep 1, 2026 25
ጎንደር፤ ነሐሴ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እና የሥርዓተ-ምግብ ችግርን በመቅረፍ ረገድ አበረታች ውጤት ማስገኘቱን የአማራ ክልል እንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ያለበትን ደረጃ እና በምርት አቅርቦት ረገድ እያስገኘ ያለውን ውጤት በጎንደር ከተማ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሁነኛው በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የሥርዓተ-ምግብን ለማሻሻል የሌማት ትሩፋትን በስፋት የመተግበር ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። መርሃ ግብሩ በቂ ምርት ለማቅረብ፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የሚያስችል ውጤት ማስገኘቱንም ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የበጀት ዓመትም ከ1 ነጥብ 6 ቢሊየን በላይ እንቁላል፣ ከሁለት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ቶን በላይ ወተት እና 900 ሺህ ቶን የሥጋ ምርት በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን በማሳያነት አንስተዋል። በተጨማሪም ከ36 ሺህ ቶን በላይ ማር በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ጠቁመው፤ የዓሣ ልማቱንም በሐይቆች፣ በወንዞች እና በሰው ሠራሽ ኩሬዎች ጭምር በማስፋት አበረታች ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል። ለሌማት ትሩፋት ማነቆ የነበረውን የመኖ እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍም 46 ዘመናዊ የመኖ ማቀናበሪያ ፋብሪካዎችን ወደ ማምረት ማስገባት መቻሉንም ጠቅሰዋል። በከተሞችና አካባቢው በስፋት እየተካሄደ የሚገኘውን የሌማት ትሩፋት በቀጣይም በሁሉም የገጠር አካባቢዎች ለማስፋት የልምድ ልውውጥ እየተደረገ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። በጎንደር ከተማ አስተዳደር እንስሳትና ዓሣ ሀብት መምሪያ የኤክስቴንሽን ኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ ሀብታሙ ዘገዬ ፤ ተግባራዊ የተደረገው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በየዘርፉ ውጤት ተገኝቶበታል ብለዋል። በዘርፉ ተደራጅተው ወደ ሥራ ለገቡ ወጣቶች የብድር፣ የቦታ እና ሌሎች ድጋፎችን በመስጠት የከተማውን የእንቁላል፣ የወተትና የሥጋ አቅርቦት እጥረት በአጭር ጊዜ ማሻሻል መቻሉን አስረድተዋል። ለመጪው የአዲስ ዓመት በዓልም ከ65 ሺህ በላይ የሥጋ ዶሮ፣ 40 ሺህ የደለበ በግና ፍየል በማቅረብ ገበያውን ለማረጋጋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል። በከተማው በዶሮና ንብ እርባታ የተሰማሩት ወይዘሮ ፅላተማርያም ተመስገን እንደተናገሩት፤ በ50 ጫጩቶች የጀመሩት የዶሮ እርባታ ሥራ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓትም በሦስት ቅርንጫፎች 47 ሺህ እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማራባት በቀን እስከ 27 ሺህ የሚደርስ እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ ባደረገላቸው ድጋፍ የንብና የዓሣ ልማትን በተቀናጀ አግባብ መጀመራቸውን አመልክተው፤ በተሰማሩበት መስክም ለ137 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም ተናግረዋል። የ"ዘርፌ፣ ሀና እና ጓደኞቻቸው" ሽርክና ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሽመልስ አርጋው በበኩላቸው፤ በ45 ሺህ ብር የጀመሩትን የወተት ልማት ስራ ላይ ጠንክረው በመሥራት ውጤታማ መሆን መቻላቸውን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ቃል ኪዳን
Sep 1, 2026 87
የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎች በአፍሪካ ላይ ማረፍ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከተከታታይ የድርቅ ክስተቶች እስከ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋዎች አህጉሪቷን በከፍተኛ ሁኔታ እየተፈታተኑም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በእነዚህና በሌሎች ፈተናዎች ውስጥ የአፍሪካ አረንጓዴ ትራንስፎርሜሽን ግንባር ቀደም ተዋናይ ሆና መጥታለች። በዚህም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎችን ከወረቀት አልፎ በተግባር በመከወን ስኬታማና ተጨባጭ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። እ.አ.አ በ2011 ይፋ የሆነው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ከኢኮኖሚ እድገት ጎን ለጎን ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር እና ከካርቦን ነጻ የሆነ ኢኮኖሚን የመገንባት ውጥን ያለው ነው። ስትራቴጂውም አራት አንኳር ምሰሶዎች አሉት፦ የመጀመሪያው ዘላቂ ግብርና እና የቁም እንስሳት ውጤታማነትን ማሳደግ ሲሆን በዚህ ውስጥ ምርታማነትንና የአርሶ አደሮችን ገቢ መጨመር እንዲሁም የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ብክለትን መቀነስ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በደን ልማት አማካኝነት ለደኖች ጥበቃ ማድረግ፣ የደን መልሶ ልማት እና ካርቦንን አምቆ መያዝ የሚያስችሉ ግዙፍ አረንጓዴ ፕሮጀክቶችን ወደ ትግበራ ማስገባት ሁለተኛው ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ነው። የሃይድሮ፣ የእንፋሎት፣ የንፋስ እና የፀሐይ ታዳሽ ኃይሎችን ማስፋፋት ሌላኛው የትኩረት ማዕከል መሆኑ በስትራቴጂክ ሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በትራንስፖርት፣ በኢንዱስትሪና በመሰረተ ልማት ግንባታዎች ዘመናዊ እና ኃይል ቆጣቢ የቴክኖሎጂ አማራጮችን መጠቀም አራተኛው ጉዳይ ነው። አረንጓዴ አሻራ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ትልቁ የተግባር ማሳያ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ እስከ አሁን ከ54 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። የአካባቢ ጥበቃ ስራ ማህበረሰብን በግልጽ በማሳተፍ በመተግበር ላይ የሚገኝ ትልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው። ኢትዮጵያ የኃይል ምንጭ አማራጮቿን ከታዳሽ ኃይል እያገኘች መሆኗም የስትራቴጂውን ስኬታማነት ያመላክታል። ብዝኃ የኢነርጂ አማራጮችን መጠቀም ከብክለት ነጻ የኃይል አቅርቦት እንዲገኝ እያደረገ ነው። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ትውልድን የሚሻገር ሁሉን አቀፍ እሳቤ ሲሆን፤ ስትራቴጂው የኢኮኖሚ እድገትን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ያስተሳሰረና የብክለት ቅነሳን የሚያረጋግጥም ነው። በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን ከመትከል እስከ የታዳሽ የኃይል ምንጭን ማስፋት የኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት እመርታ በተግባር ገልጣ ማሳየት እያስቻላትም ይገኛል።
አርሰናል ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ
Sep 1, 2026 139
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል አስቶንቪላ 1 ለ ዐ አሸንፏል። ማምሻውን በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቡካዮ ሳካ በ59ኛው ደቂቃ ግቧን አስቆጥሯል። የ24 ዓመቱ የክንፍ መስመር ተጫዋች በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እምብዛም ግልጽ የግብ እድሎች ባልተፈጠሩበት ጨዋታ አርሰናል ያገኘውን የግብ እድል በሚገባ ተጠቅሟል። አስቶንቪላ ወደ አርሰናል የግብ ክልል በተደጋጋሚ ጊዜ ቢደርስም ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ማድረግ ተስኖታል። በ75 ሚሊዮን ፓውንድ ከኒውካስትል ዩናይትድ ወደ አርሰናል የተዘዋወረው ብሩኖ ጉማራይሽ ተቀይሮ በመግባት የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ተከታታይ ድሉን አግኝቷል። በአንጻሩ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት በርካታ ቁልፍ ተጫዋቾቹን ያጣው አስቶንቪላ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል። አስቶንቪላ በሁለቱ የሊግ ጨዋታዎች ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ማድረግ አልቻለም። በሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶንቪላ ከአዲስ አዳጊው ሁል ሲቲ ጋር ይጫወታል። በለንደን ደርቢ አርሰናል ከቼልሲ የሚያደርገው ጨዋታ ከወዲሁ ተጠባቂ ነው። የሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳሉ።
ሀገራዊ ምክክሩ በመደማመጥ ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው- የጉባኤው ተሳታፊዎች
Aug 31, 2026 277
ጎንደር ፤ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ) ፡-ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያዊያን በመደማመጥና በመመካከር ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው ሲሉ የምክክር ጉባኤው ተሳታፊዎች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለመጀመሪያ ጊዜ አካታችና አሳታፊ በሆነ መልኩ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሰባስቦ በመምከር አዲስ የታሪክ ምእራፍ የተከፈተበት መሆኑ ይታወቃል። በዚሁ የምክክር ጉባኤ ህዝብን የወከሉ 4 ሺህ ተሳታፊዎች በምክክር ኮሚሽኑ በተለዩ ስምንት የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር በስኬት አጠናቀዋል። በዚሁ መርሃ ግብር የመዝጊያ ስነ ስርአት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገር ጥላ ስር በሀሳቦች ላይ በመምከር ችግሮችን በመፍታት ሀገር መገንባት እንደሚችሉ ያሳዩበት መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ ችግሮችን ከመፍታትም ባለፈ ለፖለቲካ ልምምድና የሀገር ግንባታ ጠንካራ መሰረት የሚያኖር መሆኑንም አንስተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጉባኤው ተሳታፊዎች ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያዊያን በመደማመጥና በመመካከር ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የሽማግሌዎች መማክርት ጉባኤ አባልና የምክክር ኮሚሽኑ የአማካሪ ኮሚቴ አባል አቶ ባዩ በዛብህ፤ የምክክሩ ሂደት ዜጎች ለሀገራቸው ዘላቂ ሰላምና እድገት በማሰብ በትኩረትና በጥልቀት የመከሩበት መሆኑን ገልጸዋል። በጉዳዮች ላይ መመካከር ሲቻል ከሚነጣጠሉ ይልቅ የሚያቀራርቡ በርካታ የጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች እንዳሉ በተግባር የታየበት ስለመሆኑም አንስተዋል። ሀገራዊ ተግዳሮቶችን በመሳሪያና በጉልበት ሳይሆን በሰለጠነ አግባብ በምክክር የመፍታት አዲስ ባህል የተፈጠረበት ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑንም አስረድተዋል። ህብረተሰቡም የምክክሩን ውጤቶችና በምክክሩ የተደረሰባቸውን መደምደሚያዎች መሰረት በማድረግ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን መቀበልና መተግበር እንደሚገባው አሳስበዋል።   ሌላኛው የምክክር ጉባኤው ተሳታፊ የነበሩት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሶሺዮሎጂ መምህርና የፖሊሲና ስትራቴጂ ጥናት አስተባባሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሀቢብ ሰይድ፤ የምክክር ሂደቱ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ውጭ ድጋፍና ጣልቃ ገብነት በራስ አቅም የተካሄደ በመሆኑ ታሪካዊ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ምክክሩ ማንኛውም ተሳታፊ ያለ ምንም ተፅዕኖና ጫና ሀሳቡን በነፃነት ያራመደበት፣ በቀረቡ ሃሳቦች ላይ በነፃነት በመከራከር በሃሳብ የበላይነት በመተማመን የተካሄደ ነበር ብለዋል። እንደ አጠቃላይ የምክክር ሂደቱ በዚህ ዘመን ግጭትና ጦርነት አስፈላጊ አለመሆኑንና በምክክር የትኛውንም ችግር መፍታት እንደሚቻል በተግባር የታየበት ስለመሆኑ አስረድተዋል። በመሆኑም ከምክክሩ የተገኙ ውጤቶችን በቀጣይነት ተግባራዊ በማድረግ የሀገርን ችግሮች በዘላቂነት መፍታት የሁላችንም አደራና ሃላፊነት ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል።    
የሚታይ
21ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ ይከበራል-አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር
Sep 1, 2026 63
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2018 (ኢዜአ)፦21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሕዝቦችን ትስስርና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ እንደሚከበር የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። የ21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ በበዓሉ መሪ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ እያካሔደ ይገኛል። በውይይት መድረኩ የሁሉም ክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች አፈ-ጉባዔዎች፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች፣ሚኒስትሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የዘንድሮው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ኢትዮጵያ ያካሔደችው ስኬታማ ሀገራዊ ምርጫ እና ሀገራዊ ምክክር በውጤታማነት በተጠናቀቀበት ማግሥት መሆኑ ከወትሮው ለየት ያደርገዋል። በዓሉ በሕዝቦች መካከል የሚደረጉ ባሕላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልውውጦችን በማስፋት ዘላቂ መከባበርና አብሮነትን ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የበዓሉ ዝግጅት በየደረጃው ከሚገኙ ማኅበረሰቦች ጋር በመቀናጀት ሕዝባዊ መሠረቱን የጠበቀና ሕብረ-ብሔራዊ ውበቱን በሚገልጽ መልኩ እንዲከበር አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። 21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሕዝቦችን ትስስርና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ እንደሚከበር ጠቅሰው፤ ለዚህም ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዓሉ በክልሎች፣በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በፌዴራል ተቋማት፣ ከሀገር ውጭ በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ሲከበር ቆይቶ ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ማጠቃለያው ይሆናል።
የአማራ ክልልን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅና ልማትን ለማስቀጠል የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Aug 31, 2026 277
ባህርዳር ፤ ነሀሴ 25/2018 (ኢዜአ) ፦የአማራ ክልልን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅና ልማትን ለማስቀጠል የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት ሥራ አፈጻጸም እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ላይ ያተኮረ መድረክ የክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።   በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እንደተናገሩት የክልሉን ሰላምና ጸጥታን ለማስጠበቅና ልማት ለማሳለጥ የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ለዚህም በየደረጃው ያሉ አመራሮች ህብረተሰቡን በማሳተፍ የላቀ ሚናቸውን ይበልጥ እንዲወጡ አስገንዝበዋል። አመራሩ ህዝብን በቁርጠኝነት በማገልገል በትብብር የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ከዳር ማድረስ አለበት ሲሉ አሳስበዋል። የክልሉ ሕዝብ ከመንግስት ጎን ሆኖ ጽንፈኞችን በመዋጋት በልማትና በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑንም አንስተዋል። በቀጣይም የክልሉን ሕዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ከመቼውም ጊዜ በላይ በቅንጅት እንደሚሰራ ርዕሰ መስተዳድሩ አጽኖት ሰጥተዋል።
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ ዐቅም እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ኢትዮጵያ አካታች ልማት እያረጋገጠች መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው
Aug 31, 2026 279
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25 /2018 (ኢዜአ)፦የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ ዐቅም እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ኢትዮጵያ አካታች ልማት እያረጋገጠች መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ተገኝተው የተቋሙን የሪፎርም ስራዎች ተመልክተዋል። ከጉብኝቱ በኋላ ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የተከናወነው ሪፎርም የሥራ ቦታዎችን ከማሻሻል ባለፈ፣ የሥራ ባህልን፣ የአገልግሎት ጥራትንና ተቋማዊ ዐቅምን የሚያጎለብት አዎንታዊ ለውጥ መሆኑን ገልጸዋል።   የአገልግሎቱ አመራሮች፣ ሠራተኞችና ስደተኞች በመቀናጀት በዋና መሥሪያ ቤቱ፣ በ6 ክልሎች በሚገኙ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶችና በ27 መጠለያ ጣቢያዎች ያከናወኑት ሥራ በራስ ዐቅም ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ያሳየ ጥሩ ተሞክሮ መሆኑንም ጠቁመዋል። በተለይም የመደመር መንግሥት የግብርና እመርታ ማሳያ የሆነውን የሌማት ትሩፋት በመጠቀም በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በዶሮና እንስሳት እርባታ፣ በንብ ማነብና በተለያዩ የዕጽዋት ልማት ዘርፎች የተጀመሩ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህ ስኬት ተቋማዊ ሪፎርም የሚለካው በተሻለ የሥራ አካባቢ ብቻ ሳይሆን በሚፈጥረው ምርታማነትና ውጤት ጭምር መሆኑን ያረጋገጠ እንደሆነም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ዓለም አቀፍ ስደተኞችን በመቀበል፣ መብትና ክብራቸውን በማስጠበቅ እንዲሁም ከተቀባዩ ማኅበረሰብ ጋር በማስተሣሠር በልማት ዕድሎች ተጠቃሚ እያደረገች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።   አክለውም ስደተኞቹ የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ መሆናቸው ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፏቸውን በእጅጉ እያሳደገው ይገኛል ብለዋል። በራስ ዐቅም የሚመጣ ለውጥ የተቋምን ዐቅም እንደሚያጎለብትና ይህም የሀገርን ዐቅም እንደሚገነባ ጠቁመው፤ በስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት የታየው ስኬታማ ጉዞ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የመዲናዋ የአመራር አባላት በቁርጠኝነት ሊተጉ ይገባል
Aug 31, 2026 286
አዲስ አበባ ፣ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የመዲናዋ የአመራር አባላት በቁርጠኝነት ሊተጉ እንደሚገባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት እና በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ላለፉት ሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ውይይት አጠናቋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በውይይቱ ማጠቃለያ ባስተላለፉት የሥራ መመሪያ፤ መዲናዋን የብልጽግና ተምሳሌት የሚያደርጉ ተጨባጭ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተሻለ አቅም የመፈጸም ልምድ እየጎለበተ መሆኑን ገልጸው፤ በውጤታማ የሀብት አጠቃቀም የተመደበው ገንዘብ ለታለመለት ዓላማ በማዋል የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል ብለዋል። የሙሉ ቀን ሥራ ባህል እየሆነ መምጣቱን በማንሳት፤ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመለወጥ ዜጎቸን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ገቢራዊ በማድረግ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋለውን የመልካም አስተዳደር ችግር በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል ውጤት ተገኝቷል ብለዋል። በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ በመንገድ፣ በጤና፣ ትምህርት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ በወንዝ ዳርቻዎችና ኮሪደር ልማት ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎቸን ለማከናወን ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል። በመሆኑም አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የመዲናዋ የአመራር አባላት በቁርጠኝነት ሊተጉ ይገባል ብለዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጃንጥራር ዓባይ በበኩላቸው፤ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት የአመራር አባላት የጋራ ግንዛቤ በመያዝ የለውጥ ርምጃዎችን መጀመር እንዳለባቸው ገልጸዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ዲሞክራሲ ስርዓት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ እንዳሉት፣ህዝቡ በምርጫው የሰጠንን ተጨማሪ ዕድል በልማት ለመካስ ለቀጣይ ተልዕኮ ራሳችንን ማዘጋጀት ይገባናል ብለዋል።
የአማራ ክልል ሕዝብ ጽንፈኝነትን በመታገል በክልሉ በሁሉም መስኮች ውጤት እንዲመዘገብ እያደረገ ያለው ስራ የሚበረታታ ነው
Aug 31, 2026 285
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25 /2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ሕዝብ ጽንፈኝነትን በመታገል በክልሉ በሁሉም የልማት መስኮች ውጤት እንዲመዘገብ እያደረገ ያለው ስራ ምስጋና የሚቸረው ነው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።   በመድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ የአማራ ክልል ሕዝብ ለሀገር አንድነት፣ ለሥርዓተ መንግሥት መከበር እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ዋጋ ሲከፍል የኖረ፣ አሁንም እየከፈለ ያለ መሆኑን ተናግረዋል። ችግር ቢኖር እንኳን በሕግ አግባብ እንዲፈታ የሚጠይቅ፣ ለሕግ መከበር ቅድሚያ የሚሰጥ እና ለሀገር ሉዓላዊነት መከበር ቀናኢ የሆነ ሕዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡ በ2018 በጀት ዓመት ጽንፈኝነትን መታገሉን ገልፀው፤ የጸጥታ ኀይሉ እንዲጠናከር፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበር የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሕዝቡ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ባለው ቀናኢ አስተሳሰብ ምርጫን በአግባቡ በማካሄድ የሚሆነውን እንደራሴ መምረጡን አንስተዋል። በክልሉ በፈተና ውስጥ ሆኖም ከፍተኛ የሆነ ልማት እንዳለም ገልጸዋል።ክልሉ የብልጽግናን እሳቤ በአግባቡ እየተገበረ መሆኑንም አንስተዋል።የክልሉ ሕዝብ መንግሥት ለሚተገብራቸው ተግባራት ሁሉ ተባባሪ እንደሆነም ገልጸዋል።የክልሉ ሕዝብ ለሠራነው ሥራ ዕውቅና ይሰጠናል፤ችግሮች ሲኖሩ ደግሞ በግልጽ ይናገራል ነው ያሉት። በነጠላ ትርክት እና በጽንፈኝነት ላይ የተመሠረተ፣በትናንት በደሎች ላይ የተቸነከረ ፣ የሴራ ትንታኔ ያለበት እና ተቋማትን የሚበላ የፖለቲካ አካሄድ ለሀገር እና ለሕዝብ እንደማይጠቅምም ተናግረዋል።   ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር የጋራ አሻራ እና ታሪክ እንዲኖር እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።የጋራ ታሪክ እና አሻራ አስቦ መሥራት ሲቻል ጠንካራ ፓርቲ፣ ጠንካራ መንግሥት እና ጠንካራ ሀገር መፍጠር ይቻላል ብለዋል። ጠንካራ ክልላዊ የሕግ ማስከበር ሥራ መሥራት ይጠበቃል ያሉት አቶ አደም የክልሉን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ሁኔታውን መገምገም እና መረጃ ላይ የተመሠረተ የሕግ ማስከበር ሥራን መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል። የፌዴራል መንግሥት እና ብልጽግና ፓርቲ ክልሉ በሚፈልገው ጉዳይ ሁሉ ከጎኑ መኾናቸውንም አስታውቀዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
21ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ ይከበራል-አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር
Sep 1, 2026 63
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2018 (ኢዜአ)፦21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሕዝቦችን ትስስርና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ እንደሚከበር የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። የ21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ በበዓሉ መሪ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ እያካሔደ ይገኛል። በውይይት መድረኩ የሁሉም ክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች አፈ-ጉባዔዎች፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች፣ሚኒስትሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የዘንድሮው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ኢትዮጵያ ያካሔደችው ስኬታማ ሀገራዊ ምርጫ እና ሀገራዊ ምክክር በውጤታማነት በተጠናቀቀበት ማግሥት መሆኑ ከወትሮው ለየት ያደርገዋል። በዓሉ በሕዝቦች መካከል የሚደረጉ ባሕላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልውውጦችን በማስፋት ዘላቂ መከባበርና አብሮነትን ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የበዓሉ ዝግጅት በየደረጃው ከሚገኙ ማኅበረሰቦች ጋር በመቀናጀት ሕዝባዊ መሠረቱን የጠበቀና ሕብረ-ብሔራዊ ውበቱን በሚገልጽ መልኩ እንዲከበር አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። 21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሕዝቦችን ትስስርና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ እንደሚከበር ጠቅሰው፤ ለዚህም ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዓሉ በክልሎች፣በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በፌዴራል ተቋማት፣ ከሀገር ውጭ በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ሲከበር ቆይቶ ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ማጠቃለያው ይሆናል።
ሀገራዊ ምክክሩ በመደማመጥ ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው- የጉባኤው ተሳታፊዎች
Aug 31, 2026 277
ጎንደር ፤ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ) ፡-ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያዊያን በመደማመጥና በመመካከር ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው ሲሉ የምክክር ጉባኤው ተሳታፊዎች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለመጀመሪያ ጊዜ አካታችና አሳታፊ በሆነ መልኩ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሰባስቦ በመምከር አዲስ የታሪክ ምእራፍ የተከፈተበት መሆኑ ይታወቃል። በዚሁ የምክክር ጉባኤ ህዝብን የወከሉ 4 ሺህ ተሳታፊዎች በምክክር ኮሚሽኑ በተለዩ ስምንት የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር በስኬት አጠናቀዋል። በዚሁ መርሃ ግብር የመዝጊያ ስነ ስርአት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገር ጥላ ስር በሀሳቦች ላይ በመምከር ችግሮችን በመፍታት ሀገር መገንባት እንደሚችሉ ያሳዩበት መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ ችግሮችን ከመፍታትም ባለፈ ለፖለቲካ ልምምድና የሀገር ግንባታ ጠንካራ መሰረት የሚያኖር መሆኑንም አንስተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጉባኤው ተሳታፊዎች ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያዊያን በመደማመጥና በመመካከር ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የሽማግሌዎች መማክርት ጉባኤ አባልና የምክክር ኮሚሽኑ የአማካሪ ኮሚቴ አባል አቶ ባዩ በዛብህ፤ የምክክሩ ሂደት ዜጎች ለሀገራቸው ዘላቂ ሰላምና እድገት በማሰብ በትኩረትና በጥልቀት የመከሩበት መሆኑን ገልጸዋል። በጉዳዮች ላይ መመካከር ሲቻል ከሚነጣጠሉ ይልቅ የሚያቀራርቡ በርካታ የጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች እንዳሉ በተግባር የታየበት ስለመሆኑም አንስተዋል። ሀገራዊ ተግዳሮቶችን በመሳሪያና በጉልበት ሳይሆን በሰለጠነ አግባብ በምክክር የመፍታት አዲስ ባህል የተፈጠረበት ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑንም አስረድተዋል። ህብረተሰቡም የምክክሩን ውጤቶችና በምክክሩ የተደረሰባቸውን መደምደሚያዎች መሰረት በማድረግ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን መቀበልና መተግበር እንደሚገባው አሳስበዋል።   ሌላኛው የምክክር ጉባኤው ተሳታፊ የነበሩት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሶሺዮሎጂ መምህርና የፖሊሲና ስትራቴጂ ጥናት አስተባባሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሀቢብ ሰይድ፤ የምክክር ሂደቱ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ውጭ ድጋፍና ጣልቃ ገብነት በራስ አቅም የተካሄደ በመሆኑ ታሪካዊ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ምክክሩ ማንኛውም ተሳታፊ ያለ ምንም ተፅዕኖና ጫና ሀሳቡን በነፃነት ያራመደበት፣ በቀረቡ ሃሳቦች ላይ በነፃነት በመከራከር በሃሳብ የበላይነት በመተማመን የተካሄደ ነበር ብለዋል። እንደ አጠቃላይ የምክክር ሂደቱ በዚህ ዘመን ግጭትና ጦርነት አስፈላጊ አለመሆኑንና በምክክር የትኛውንም ችግር መፍታት እንደሚቻል በተግባር የታየበት ስለመሆኑ አስረድተዋል። በመሆኑም ከምክክሩ የተገኙ ውጤቶችን በቀጣይነት ተግባራዊ በማድረግ የሀገርን ችግሮች በዘላቂነት መፍታት የሁላችንም አደራና ሃላፊነት ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል።    
የአማራ ክልልን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅና ልማትን ለማስቀጠል የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Aug 31, 2026 277
ባህርዳር ፤ ነሀሴ 25/2018 (ኢዜአ) ፦የአማራ ክልልን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅና ልማትን ለማስቀጠል የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት ሥራ አፈጻጸም እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ላይ ያተኮረ መድረክ የክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።   በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እንደተናገሩት የክልሉን ሰላምና ጸጥታን ለማስጠበቅና ልማት ለማሳለጥ የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ለዚህም በየደረጃው ያሉ አመራሮች ህብረተሰቡን በማሳተፍ የላቀ ሚናቸውን ይበልጥ እንዲወጡ አስገንዝበዋል። አመራሩ ህዝብን በቁርጠኝነት በማገልገል በትብብር የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ከዳር ማድረስ አለበት ሲሉ አሳስበዋል። የክልሉ ሕዝብ ከመንግስት ጎን ሆኖ ጽንፈኞችን በመዋጋት በልማትና በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑንም አንስተዋል። በቀጣይም የክልሉን ሕዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ከመቼውም ጊዜ በላይ በቅንጅት እንደሚሰራ ርዕሰ መስተዳድሩ አጽኖት ሰጥተዋል።
የአማራ ክልል ሕዝብ ጽንፈኝነትን በመታገል በክልሉ በሁሉም መስኮች ውጤት እንዲመዘገብ እያደረገ ያለው ስራ የሚበረታታ ነው
Aug 31, 2026 285
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25 /2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ሕዝብ ጽንፈኝነትን በመታገል በክልሉ በሁሉም የልማት መስኮች ውጤት እንዲመዘገብ እያደረገ ያለው ስራ ምስጋና የሚቸረው ነው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።   በመድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ የአማራ ክልል ሕዝብ ለሀገር አንድነት፣ ለሥርዓተ መንግሥት መከበር እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ዋጋ ሲከፍል የኖረ፣ አሁንም እየከፈለ ያለ መሆኑን ተናግረዋል። ችግር ቢኖር እንኳን በሕግ አግባብ እንዲፈታ የሚጠይቅ፣ ለሕግ መከበር ቅድሚያ የሚሰጥ እና ለሀገር ሉዓላዊነት መከበር ቀናኢ የሆነ ሕዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡ በ2018 በጀት ዓመት ጽንፈኝነትን መታገሉን ገልፀው፤ የጸጥታ ኀይሉ እንዲጠናከር፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበር የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሕዝቡ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ባለው ቀናኢ አስተሳሰብ ምርጫን በአግባቡ በማካሄድ የሚሆነውን እንደራሴ መምረጡን አንስተዋል። በክልሉ በፈተና ውስጥ ሆኖም ከፍተኛ የሆነ ልማት እንዳለም ገልጸዋል።ክልሉ የብልጽግናን እሳቤ በአግባቡ እየተገበረ መሆኑንም አንስተዋል።የክልሉ ሕዝብ መንግሥት ለሚተገብራቸው ተግባራት ሁሉ ተባባሪ እንደሆነም ገልጸዋል።የክልሉ ሕዝብ ለሠራነው ሥራ ዕውቅና ይሰጠናል፤ችግሮች ሲኖሩ ደግሞ በግልጽ ይናገራል ነው ያሉት። በነጠላ ትርክት እና በጽንፈኝነት ላይ የተመሠረተ፣በትናንት በደሎች ላይ የተቸነከረ ፣ የሴራ ትንታኔ ያለበት እና ተቋማትን የሚበላ የፖለቲካ አካሄድ ለሀገር እና ለሕዝብ እንደማይጠቅምም ተናግረዋል።   ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር የጋራ አሻራ እና ታሪክ እንዲኖር እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።የጋራ ታሪክ እና አሻራ አስቦ መሥራት ሲቻል ጠንካራ ፓርቲ፣ ጠንካራ መንግሥት እና ጠንካራ ሀገር መፍጠር ይቻላል ብለዋል። ጠንካራ ክልላዊ የሕግ ማስከበር ሥራ መሥራት ይጠበቃል ያሉት አቶ አደም የክልሉን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ሁኔታውን መገምገም እና መረጃ ላይ የተመሠረተ የሕግ ማስከበር ሥራን መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል። የፌዴራል መንግሥት እና ብልጽግና ፓርቲ ክልሉ በሚፈልገው ጉዳይ ሁሉ ከጎኑ መኾናቸውንም አስታውቀዋል።
በክልሉ የህዝቦችን አብሮነት በማረጋገጥ ዘላቂ ሰላም የማጽናት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Aug 31, 2026 290
ሆሳዕና፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሕዝቦችን አብሮነትና የሰላም እሴቶች በማጎልበት ዘላቂ ሰላምን የማጽናት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። "ዘላቂ ሰላማችን ለሁለንተናዊ ብልፅግናችን" በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ መንግስት ፀጥታ ምክር ቤት የተዘጋጀ ዓመታዊ ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የህዝቦችን አብሮነት በማጠናከር የሰላም እሴት ግንባታን ለማጎልበት የተጀመረው ቅንጅታዊ ሥራ ይጠናከራል፡፡ ለዚህም የሰላምና ፀጥታ ማዕከላትን በማጠናከር ህገ ወጥነትን የመከላከል፣ ከፋፋይ አስተሳሰቦችን የማረምና ህግ የማስከበር ስራ ትኩረት እንደተሰጠውም ጠቁመዋል። የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት አባላት የክልሉን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ የሚከናወኑ ተግባራትን በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል። ዘላቂ ሰላም ለማስፈን የጋራ ትብብር ያሻል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ማህበረሰቡ የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበትና የዚህ ድምር ውጤት በዘላቂ ሰላም ላይ የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በበኩላቸው፣ በክልሉ በተለያየ መንገድ የሚከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ሀይማኖታዊና ባህላዊ እሴቶችን ጭምር በመጠቀም እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ህዝቡ ችግሮችን በመነጋገርና በመወያየት የመፍታት ባህሉን እያጎለበተ መምጣቱን ጠቁመዋል። የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት አባላት በየአካባቢው ያሉ የሰላም እሴቶችን በመጠቀም ሰላምን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለውን ጥረት ማጠናከር እንዳለባቸውም ገልፀዋል።   የክልሉ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢና የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ መልከፀዴቅ በሰጡት አስተያየት በክልሉ አብሮነትን በማጠናከር ሰላምን ለማጽናት በተሰሩ ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። የክልሉ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለዚህ ስኬት ከመንግሥት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱንና ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚያስቀጥልም ጠቁመዋል። የክልሉ የባህል ሽማግሌዎች ፎረም ሰብሳቢ ዳኛ ሞላ በለጠ እንደገለፁት በክልሉ የወንድማማችነትና የእህትማማችነት እሴቶችን ለማጠናከር እንሰራለን ብለዋል። ባህላዊ የሽምግልና ስነ ሥርዓትን ለዘላቂ ሰላም ግንባታና ለህዝቦች አንድነት መጠናከር ለማዋል የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑንና ተግባሩን አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ አስረድተዋል። በመርሐ ግብሩ የክልሉ፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የፀጥታ ዘርፍ እንዲሁም የክልሉ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከፍተኛ አመራሮች፣ የምክር ቤቱ አባላት፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የባህል ሽማግሌዎችና ወጣቶች ተሳትፈዋል።
የምክክር ጉባዔው ኢትዮጵያ በህዝቦቿ አንድነት የምታሸንፍ ሀገር መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው
Aug 31, 2026 326
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያ በህዝቦቿ አንድነት የምታሸንፍ ሀገር መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው ሲሉ በጉባዔው ላይ የተሳተፉ ተመካካሪዎች ገለጹ። ጉባኤው የምክክር ባህልን ያዳበረና የሀገሪቷን የፖለቲካ ባህል ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ታሪካዊ ክስተት መሆኑንም ተናግረዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ተመካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ አሳታፊ፣ ግልጽና አካታች በሆነ መልኩ የተከናወነው፤ ኢትዮጵያውያን ችግራቸውን በራሳቸው መፍታት እንደሚችሉ ያረጋገጡበት መሆኑን ጠቁመዋል። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል አቶ ጉዮ ዋሪዮ እንደተናገሩት፤ የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሀሳብ ልዩነቶችን በግጭትና ጠመንጃ ለመፍታት ይደረግ የነበረውን የታሪክ አዙሪት በመቀየር አዲስ የፖለቲካ ባህልን የገነባ ነው። በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያውያን ያለምንም ገደብና ስጋት ለሀገራቸው ይበጃል ያሉትን ሀሳብ በነጻነት ማዋጣታቸውን ተናግረዋል። ሂደቱም ኢትዮጵያውያን ተነጋግረውና ተማክረው የመግባባት ባህላቸውን በተግባር ያሳዩበት፣ እንዲሁም እርስ በእርስ የተማማሩበትና ሀገራቸውን ያወቁበት ነው ብለዋል። በምክክሩ ሂደት ከውጭና ከውስጥ ያሉ የኢትዮጵያ ጠላቶችና ተላላኪዎቻቸው በማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማድረግ ሂደቱን ለማስተጓጎል ቢሞክሩም በኢትዮጵያውያን አሸናፊነት በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ገብሩ በርሄ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ኢትዮጵያውያን በጋራ ሀሳብ ላይ እንዲሰባሰቡ ማስቻሉን ተናግረዋል። አራት ሺህ የሚደርሱ ተሳታፊዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። ይህ የምክክር መድረክ "ትንሽዋ ኢትዮጵያ" ተብሎ ሊገለጽ የሚችልና የሀገሪቷን ብዝሃነት በአንድነት ያንጸባረቀ መሆኑንም አብራርተዋል። ተሳታፊዎች ያለምንም ተጽዕኖና በሙሉ ፍላጎታቸው ምክር ሀሳቦችን ማቅረብ መቻላቸውን ተናግረዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ በምክክር እና በህዝቦቿ አንድነት የምታሸንፍ ሀገር መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው ሲሉ ገልጸዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ መሐመድ ቦሩ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን ያሳተፈና ሀሳቦቻቸውን በነጻነት እንዲያዋጡ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ "ኢትዮጵያ አሸንፋለች" ያሸነፈችበት ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። ይህ የጋራ ተሳትፎና የምክክር ሂደት ሀገሪቷን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግርና የአንድነቷን መሰረት የሚያጠናክር መሆኑን አመላክተዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ በማድረጋቸውና የጋራ ሀሳብ በማንሸራሸራቸው ምክንያት የምክክር ሂደቱ ውጤታማ መሆኑና የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያረጋገጠ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያውያን ያለ ሶስተኛ ወገን ጣልቃ ገብነት በጋራ አጀንዳዎች ላይ እንዲመክሩ በማድረግ ረገድ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የውክልና ጦርነትና የቪዲዮ ዘመቻዎችን ሲያካሂዱ የነበሩ አካላት ኢትዮጵያውያን ተቀራርበው መመካከራቸው እንዳስደነገጣቸው ተናግረዋል። ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲመክሩና ሲነጋገሩ የማይፈቱት ችግር እንደሌለ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በተግባር አረጋግጧል ብለዋል።  
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሰላም ባለቤትነት የመዲናዋ ሰላምና ደኅንነት ይበልጥ እንዲጠናከር አስችሏል
Aug 31, 2026 328
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን የሰላም ባለቤትነትና የጸጥታ ኃይሎችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማጠናከር ሰላምና ደኅንነት ይበልጥ ማረጋገጥ መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በየደረጃው ባሉ የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች ውይይት ተደርጎበት ዛሬ ይጠናቀቃል። በአምስት ዓመቱ ዕቅድ በከተማ ግብርና፣ በቤቶች ግንባታ፣ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በሌሎች ሰው ተኮር ሥራዎች የመዲናዋን ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ተግባራት ለማከናወን የሚያስችል የጋራ መግባባት ላይ ይደረሳል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተቋማት ያለፈውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሚገባ በመፈጸም ያሳዩትን ቁርጠኝነት በቀጣዮቹ ዓመታትም አጠናክረው እንዲቀጥሉ ግልጽና ሊያሰራ የሚችል ዕቅድ ነድፈው እንዲንቀሳቀሱ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የነዋሪዎችን የሰላም ባለቤትነትና የጸጥታ ኃይሎችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማጠናከር የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት ይበልጥ ማጠናከር ተችሏል። ሕዝቡን ያሳተፈ የጸጥታ ሥራ በማከናወን ሕገ ወጥ ተግባራትን የሚጠየፍ ማኅበረሰብ በመፍጠር መዲናዋ የሰላም ደሴት እንድትሆን ተደርጓል ብለዋል። አዲስ አበባ ዘላቂና አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ለማስቻል የመዲናዋ የሰላም ሠራዊት አደረጃጀት ገንቢ ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡን የሰላሙ ባለቤት በማድረግ ለእያንዳንዱ ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ ከጸጥታ ኃይሎች ጋር በቅንጅት የሚሰራበት አውድ ተፈጥሯል ብለዋል። ወንጀል ፈጽመው ለማምለጥ የሚሞክሩ ኃይሎችን በቀላሉ ለመቆጣጠር ከሸገር ሲቲ አስተዳደር ጋር በቅንጅት በመሥራት ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። በቀጣይም አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ አደራ በላቀ ደረጃ ለመፈጸም የሰላም፣ የጸጥታና ደህንነት ሥራ ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል። በዚህም የወንጀል ምጣኔን መቀነስ፣ የዜጎችን የሰላም ባለቤትነት ሚና ማላቅ፣ ልዩነቶችን በንግግር የሚፈታ ማኅበረሰብ በመፍጠር በሰላም እሴት ግንባታ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ሕገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ፣ የመሬት ወረራና ሕገ ወጥ ግንባታ እንዲሁም ሌሎች ወንጀሎችን በመቆጣጠር የሕግ የበላይነት የተረጋገጠባት መዲና የማድረግ ራዕይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የአፍሪካ የሰላምና ደኅንነት መዋቅር አስቸኳይ ማሻሻያ ያስፈልገዋል - መሐመድ አሊ የሱፍ
Aug 30, 2026 540
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ የሰላምና ደኅንነት መዋቅር በአስተማማኝ የገንዘብ ምንጭ የሚመራ አስቸኳይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐመድ አሊ የሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ኅብረት 21ኛውን አህጉራዊ ልዩ የግጭት መከላከልና አፈታት ጉባዔ በአንጎላ መዲና ሉዋንዳ አካሂዷል።   የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በጉባዔው ላይ እንዳሉት፤ የአፍሪካ የሰላምና ደኅንነት መዋቅር በአህጉሪቷ እየተደቀኑ ካሉ ሥጋቶች አኳያ አስቸኳይ ማሻሻያ ያስፈልገዋል። በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ እየታዩ የመጡት ቀጣይነት ያላቸው ቀውሶች የአህጉሪቷ ዋነኛ የሰላምና ደኅንነት ሥጋቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። ሽብርተኝነት፣ የጽንፈኝነት ጥቃት፣ የባሕር ላይ ዝርፊያ፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀልና ስደተኞችን አላግባብ ማስተናገድ የመሳሰሉ ሥጋቶች የአፍሪካ ሀገራት የጋራ እርምጃ እንዲወስዱ የሚጠይቁ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሊቀ መንበሩ ግጭትን መከላከል የኅብረቱ ቀዳሚ ትኩረት መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። የተጠናከረ አህጉራዊ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት፣ የኅብረቱ ውሳኔዎችን በተሻለ ሁኔታ መተግበርና ለሰላም ማስከበር ሥራዎች ዘላቂ የገንዘብ ምንጭ ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። ለዚህም በአስተማማኝ የገንዘብ ምንጭ የሚመራና የሚተዳደር የሰላም ፈንድ መኖሩ ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል።   ከተባበሩት መንግሥታት ጋር ያሉትን ጨምሮ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሽርክናዎች የአፍሪካን እውነታና ፍላጎት በሚያንጸባርቅ መልኩ መጠናከር እንዳለባቸውም ገልጸዋል። በተጨማሪም የኅብረቱ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማኅበረሰቦችና ቀጣናዊ ስልቶች በመከላከያ ዲፕሎማሲ ውስጥ ማዕከላዊ ሚና እንዳላቸው አጽንዖት ሰጥተዋል። በሰላምና ደኅንነት ምክር ቤት፣ በኮሚሽኑ፣ በአባል ሀገራትና በቀጣናዊ ተቋማት መካከል ቀጣይነት ያለው ምክክር ማድረግም ለጋራ ምላሽ አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል። የአፍሪካ የሰላምና ደኅንነት ሥጋቶችን አንድም ሀገር ብቻዋን መጋፈጥ እንደማትችል የሚያስገነዘቡ መሆናቸውን አብራርተዋል። ለዚህም የጋራ ሀብትን ማሰባሰብ፣ አጋርነትን ማጠናከርና በሰላምና ደኅንነት ጉዳይ የበለጠ የፓን-አፍሪካ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል። ሕገ-መንግሥታዊ ያልሆነ የመንግሥት ለውጥ የአፍሪካ ኅብረት አጥብቆ የሚኮንነውና በፅናት የሚቀጥል ግልጽ አቋም መሆኑን አንስተዋል። የኅብረቱ ልዩ ጉባዔም የአፍሪካን የሰላምና ደኅንነት ጉዳይ በጋራ በመረከብ የራሷን አቅም የምታጠናክርበት መድረክ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሊቀ መንበሩ በማጠቃለያ መልዕክታቸው፤ ይህ የረጅም ጊዜ ሥራ የማይታክት የፖለቲካ ቁርጠኝነትን የሚጠይቅ መሆኑን አስረድተዋል። ጉባዔው አፍሪካ የሰላምና ደኅንነቷን በጋራ በመረከብ የራሷን አቅም የምታጠናክርበት መፍትሔ አመላካች መድረክ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።    
ፖለቲካ
21ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ ይከበራል-አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር
Sep 1, 2026 63
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2018 (ኢዜአ)፦21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሕዝቦችን ትስስርና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ እንደሚከበር የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። የ21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ በበዓሉ መሪ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ እያካሔደ ይገኛል። በውይይት መድረኩ የሁሉም ክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች አፈ-ጉባዔዎች፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች፣ሚኒስትሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የዘንድሮው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ኢትዮጵያ ያካሔደችው ስኬታማ ሀገራዊ ምርጫ እና ሀገራዊ ምክክር በውጤታማነት በተጠናቀቀበት ማግሥት መሆኑ ከወትሮው ለየት ያደርገዋል። በዓሉ በሕዝቦች መካከል የሚደረጉ ባሕላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልውውጦችን በማስፋት ዘላቂ መከባበርና አብሮነትን ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የበዓሉ ዝግጅት በየደረጃው ከሚገኙ ማኅበረሰቦች ጋር በመቀናጀት ሕዝባዊ መሠረቱን የጠበቀና ሕብረ-ብሔራዊ ውበቱን በሚገልጽ መልኩ እንዲከበር አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። 21ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሕዝቦችን ትስስርና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ እንደሚከበር ጠቅሰው፤ ለዚህም ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዓሉ በክልሎች፣በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በፌዴራል ተቋማት፣ ከሀገር ውጭ በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ሲከበር ቆይቶ ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ማጠቃለያው ይሆናል።
ሀገራዊ ምክክሩ በመደማመጥ ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው- የጉባኤው ተሳታፊዎች
Aug 31, 2026 277
ጎንደር ፤ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ) ፡-ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያዊያን በመደማመጥና በመመካከር ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው ሲሉ የምክክር ጉባኤው ተሳታፊዎች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለመጀመሪያ ጊዜ አካታችና አሳታፊ በሆነ መልኩ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሰባስቦ በመምከር አዲስ የታሪክ ምእራፍ የተከፈተበት መሆኑ ይታወቃል። በዚሁ የምክክር ጉባኤ ህዝብን የወከሉ 4 ሺህ ተሳታፊዎች በምክክር ኮሚሽኑ በተለዩ ስምንት የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር በስኬት አጠናቀዋል። በዚሁ መርሃ ግብር የመዝጊያ ስነ ስርአት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገር ጥላ ስር በሀሳቦች ላይ በመምከር ችግሮችን በመፍታት ሀገር መገንባት እንደሚችሉ ያሳዩበት መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ ችግሮችን ከመፍታትም ባለፈ ለፖለቲካ ልምምድና የሀገር ግንባታ ጠንካራ መሰረት የሚያኖር መሆኑንም አንስተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጉባኤው ተሳታፊዎች ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያዊያን በመደማመጥና በመመካከር ችግሮችን መፍታት እንደምንችል በተግባር ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የሽማግሌዎች መማክርት ጉባኤ አባልና የምክክር ኮሚሽኑ የአማካሪ ኮሚቴ አባል አቶ ባዩ በዛብህ፤ የምክክሩ ሂደት ዜጎች ለሀገራቸው ዘላቂ ሰላምና እድገት በማሰብ በትኩረትና በጥልቀት የመከሩበት መሆኑን ገልጸዋል። በጉዳዮች ላይ መመካከር ሲቻል ከሚነጣጠሉ ይልቅ የሚያቀራርቡ በርካታ የጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች እንዳሉ በተግባር የታየበት ስለመሆኑም አንስተዋል። ሀገራዊ ተግዳሮቶችን በመሳሪያና በጉልበት ሳይሆን በሰለጠነ አግባብ በምክክር የመፍታት አዲስ ባህል የተፈጠረበት ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑንም አስረድተዋል። ህብረተሰቡም የምክክሩን ውጤቶችና በምክክሩ የተደረሰባቸውን መደምደሚያዎች መሰረት በማድረግ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን መቀበልና መተግበር እንደሚገባው አሳስበዋል።   ሌላኛው የምክክር ጉባኤው ተሳታፊ የነበሩት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሶሺዮሎጂ መምህርና የፖሊሲና ስትራቴጂ ጥናት አስተባባሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሀቢብ ሰይድ፤ የምክክር ሂደቱ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ውጭ ድጋፍና ጣልቃ ገብነት በራስ አቅም የተካሄደ በመሆኑ ታሪካዊ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ምክክሩ ማንኛውም ተሳታፊ ያለ ምንም ተፅዕኖና ጫና ሀሳቡን በነፃነት ያራመደበት፣ በቀረቡ ሃሳቦች ላይ በነፃነት በመከራከር በሃሳብ የበላይነት በመተማመን የተካሄደ ነበር ብለዋል። እንደ አጠቃላይ የምክክር ሂደቱ በዚህ ዘመን ግጭትና ጦርነት አስፈላጊ አለመሆኑንና በምክክር የትኛውንም ችግር መፍታት እንደሚቻል በተግባር የታየበት ስለመሆኑ አስረድተዋል። በመሆኑም ከምክክሩ የተገኙ ውጤቶችን በቀጣይነት ተግባራዊ በማድረግ የሀገርን ችግሮች በዘላቂነት መፍታት የሁላችንም አደራና ሃላፊነት ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል።    
የአማራ ክልልን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅና ልማትን ለማስቀጠል የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Aug 31, 2026 277
ባህርዳር ፤ ነሀሴ 25/2018 (ኢዜአ) ፦የአማራ ክልልን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅና ልማትን ለማስቀጠል የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት ሥራ አፈጻጸም እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ላይ ያተኮረ መድረክ የክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።   በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እንደተናገሩት የክልሉን ሰላምና ጸጥታን ለማስጠበቅና ልማት ለማሳለጥ የሚደረጉ ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ለዚህም በየደረጃው ያሉ አመራሮች ህብረተሰቡን በማሳተፍ የላቀ ሚናቸውን ይበልጥ እንዲወጡ አስገንዝበዋል። አመራሩ ህዝብን በቁርጠኝነት በማገልገል በትብብር የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ከዳር ማድረስ አለበት ሲሉ አሳስበዋል። የክልሉ ሕዝብ ከመንግስት ጎን ሆኖ ጽንፈኞችን በመዋጋት በልማትና በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑንም አንስተዋል። በቀጣይም የክልሉን ሕዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ከመቼውም ጊዜ በላይ በቅንጅት እንደሚሰራ ርዕሰ መስተዳድሩ አጽኖት ሰጥተዋል።
የአማራ ክልል ሕዝብ ጽንፈኝነትን በመታገል በክልሉ በሁሉም መስኮች ውጤት እንዲመዘገብ እያደረገ ያለው ስራ የሚበረታታ ነው
Aug 31, 2026 285
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25 /2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ሕዝብ ጽንፈኝነትን በመታገል በክልሉ በሁሉም የልማት መስኮች ውጤት እንዲመዘገብ እያደረገ ያለው ስራ ምስጋና የሚቸረው ነው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።   በመድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ የአማራ ክልል ሕዝብ ለሀገር አንድነት፣ ለሥርዓተ መንግሥት መከበር እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ዋጋ ሲከፍል የኖረ፣ አሁንም እየከፈለ ያለ መሆኑን ተናግረዋል። ችግር ቢኖር እንኳን በሕግ አግባብ እንዲፈታ የሚጠይቅ፣ ለሕግ መከበር ቅድሚያ የሚሰጥ እና ለሀገር ሉዓላዊነት መከበር ቀናኢ የሆነ ሕዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡ በ2018 በጀት ዓመት ጽንፈኝነትን መታገሉን ገልፀው፤ የጸጥታ ኀይሉ እንዲጠናከር፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበር የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሕዝቡ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ባለው ቀናኢ አስተሳሰብ ምርጫን በአግባቡ በማካሄድ የሚሆነውን እንደራሴ መምረጡን አንስተዋል። በክልሉ በፈተና ውስጥ ሆኖም ከፍተኛ የሆነ ልማት እንዳለም ገልጸዋል።ክልሉ የብልጽግናን እሳቤ በአግባቡ እየተገበረ መሆኑንም አንስተዋል።የክልሉ ሕዝብ መንግሥት ለሚተገብራቸው ተግባራት ሁሉ ተባባሪ እንደሆነም ገልጸዋል።የክልሉ ሕዝብ ለሠራነው ሥራ ዕውቅና ይሰጠናል፤ችግሮች ሲኖሩ ደግሞ በግልጽ ይናገራል ነው ያሉት። በነጠላ ትርክት እና በጽንፈኝነት ላይ የተመሠረተ፣በትናንት በደሎች ላይ የተቸነከረ ፣ የሴራ ትንታኔ ያለበት እና ተቋማትን የሚበላ የፖለቲካ አካሄድ ለሀገር እና ለሕዝብ እንደማይጠቅምም ተናግረዋል።   ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር የጋራ አሻራ እና ታሪክ እንዲኖር እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።የጋራ ታሪክ እና አሻራ አስቦ መሥራት ሲቻል ጠንካራ ፓርቲ፣ ጠንካራ መንግሥት እና ጠንካራ ሀገር መፍጠር ይቻላል ብለዋል። ጠንካራ ክልላዊ የሕግ ማስከበር ሥራ መሥራት ይጠበቃል ያሉት አቶ አደም የክልሉን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ሁኔታውን መገምገም እና መረጃ ላይ የተመሠረተ የሕግ ማስከበር ሥራን መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል። የፌዴራል መንግሥት እና ብልጽግና ፓርቲ ክልሉ በሚፈልገው ጉዳይ ሁሉ ከጎኑ መኾናቸውንም አስታውቀዋል።
በክልሉ የህዝቦችን አብሮነት በማረጋገጥ ዘላቂ ሰላም የማጽናት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Aug 31, 2026 290
ሆሳዕና፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሕዝቦችን አብሮነትና የሰላም እሴቶች በማጎልበት ዘላቂ ሰላምን የማጽናት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። "ዘላቂ ሰላማችን ለሁለንተናዊ ብልፅግናችን" በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ መንግስት ፀጥታ ምክር ቤት የተዘጋጀ ዓመታዊ ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የህዝቦችን አብሮነት በማጠናከር የሰላም እሴት ግንባታን ለማጎልበት የተጀመረው ቅንጅታዊ ሥራ ይጠናከራል፡፡ ለዚህም የሰላምና ፀጥታ ማዕከላትን በማጠናከር ህገ ወጥነትን የመከላከል፣ ከፋፋይ አስተሳሰቦችን የማረምና ህግ የማስከበር ስራ ትኩረት እንደተሰጠውም ጠቁመዋል። የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት አባላት የክልሉን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ የሚከናወኑ ተግባራትን በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል። ዘላቂ ሰላም ለማስፈን የጋራ ትብብር ያሻል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ማህበረሰቡ የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበትና የዚህ ድምር ውጤት በዘላቂ ሰላም ላይ የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በበኩላቸው፣ በክልሉ በተለያየ መንገድ የሚከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ሀይማኖታዊና ባህላዊ እሴቶችን ጭምር በመጠቀም እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ህዝቡ ችግሮችን በመነጋገርና በመወያየት የመፍታት ባህሉን እያጎለበተ መምጣቱን ጠቁመዋል። የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት አባላት በየአካባቢው ያሉ የሰላም እሴቶችን በመጠቀም ሰላምን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለውን ጥረት ማጠናከር እንዳለባቸውም ገልፀዋል።   የክልሉ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢና የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ መልከፀዴቅ በሰጡት አስተያየት በክልሉ አብሮነትን በማጠናከር ሰላምን ለማጽናት በተሰሩ ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። የክልሉ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለዚህ ስኬት ከመንግሥት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱንና ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚያስቀጥልም ጠቁመዋል። የክልሉ የባህል ሽማግሌዎች ፎረም ሰብሳቢ ዳኛ ሞላ በለጠ እንደገለፁት በክልሉ የወንድማማችነትና የእህትማማችነት እሴቶችን ለማጠናከር እንሰራለን ብለዋል። ባህላዊ የሽምግልና ስነ ሥርዓትን ለዘላቂ ሰላም ግንባታና ለህዝቦች አንድነት መጠናከር ለማዋል የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑንና ተግባሩን አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ አስረድተዋል። በመርሐ ግብሩ የክልሉ፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የፀጥታ ዘርፍ እንዲሁም የክልሉ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከፍተኛ አመራሮች፣ የምክር ቤቱ አባላት፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የባህል ሽማግሌዎችና ወጣቶች ተሳትፈዋል።
የምክክር ጉባዔው ኢትዮጵያ በህዝቦቿ አንድነት የምታሸንፍ ሀገር መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው
Aug 31, 2026 326
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያ በህዝቦቿ አንድነት የምታሸንፍ ሀገር መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው ሲሉ በጉባዔው ላይ የተሳተፉ ተመካካሪዎች ገለጹ። ጉባኤው የምክክር ባህልን ያዳበረና የሀገሪቷን የፖለቲካ ባህል ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ታሪካዊ ክስተት መሆኑንም ተናግረዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ተመካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ አሳታፊ፣ ግልጽና አካታች በሆነ መልኩ የተከናወነው፤ ኢትዮጵያውያን ችግራቸውን በራሳቸው መፍታት እንደሚችሉ ያረጋገጡበት መሆኑን ጠቁመዋል። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል አቶ ጉዮ ዋሪዮ እንደተናገሩት፤ የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሀሳብ ልዩነቶችን በግጭትና ጠመንጃ ለመፍታት ይደረግ የነበረውን የታሪክ አዙሪት በመቀየር አዲስ የፖለቲካ ባህልን የገነባ ነው። በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያውያን ያለምንም ገደብና ስጋት ለሀገራቸው ይበጃል ያሉትን ሀሳብ በነጻነት ማዋጣታቸውን ተናግረዋል። ሂደቱም ኢትዮጵያውያን ተነጋግረውና ተማክረው የመግባባት ባህላቸውን በተግባር ያሳዩበት፣ እንዲሁም እርስ በእርስ የተማማሩበትና ሀገራቸውን ያወቁበት ነው ብለዋል። በምክክሩ ሂደት ከውጭና ከውስጥ ያሉ የኢትዮጵያ ጠላቶችና ተላላኪዎቻቸው በማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማድረግ ሂደቱን ለማስተጓጎል ቢሞክሩም በኢትዮጵያውያን አሸናፊነት በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ገብሩ በርሄ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ኢትዮጵያውያን በጋራ ሀሳብ ላይ እንዲሰባሰቡ ማስቻሉን ተናግረዋል። አራት ሺህ የሚደርሱ ተሳታፊዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። ይህ የምክክር መድረክ "ትንሽዋ ኢትዮጵያ" ተብሎ ሊገለጽ የሚችልና የሀገሪቷን ብዝሃነት በአንድነት ያንጸባረቀ መሆኑንም አብራርተዋል። ተሳታፊዎች ያለምንም ተጽዕኖና በሙሉ ፍላጎታቸው ምክር ሀሳቦችን ማቅረብ መቻላቸውን ተናግረዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ በምክክር እና በህዝቦቿ አንድነት የምታሸንፍ ሀገር መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው ሲሉ ገልጸዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ መሐመድ ቦሩ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን ያሳተፈና ሀሳቦቻቸውን በነጻነት እንዲያዋጡ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ "ኢትዮጵያ አሸንፋለች" ያሸነፈችበት ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። ይህ የጋራ ተሳትፎና የምክክር ሂደት ሀገሪቷን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግርና የአንድነቷን መሰረት የሚያጠናክር መሆኑን አመላክተዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ በማድረጋቸውና የጋራ ሀሳብ በማንሸራሸራቸው ምክንያት የምክክር ሂደቱ ውጤታማ መሆኑና የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያረጋገጠ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያውያን ያለ ሶስተኛ ወገን ጣልቃ ገብነት በጋራ አጀንዳዎች ላይ እንዲመክሩ በማድረግ ረገድ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የውክልና ጦርነትና የቪዲዮ ዘመቻዎችን ሲያካሂዱ የነበሩ አካላት ኢትዮጵያውያን ተቀራርበው መመካከራቸው እንዳስደነገጣቸው ተናግረዋል። ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲመክሩና ሲነጋገሩ የማይፈቱት ችግር እንደሌለ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በተግባር አረጋግጧል ብለዋል።  
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሰላም ባለቤትነት የመዲናዋ ሰላምና ደኅንነት ይበልጥ እንዲጠናከር አስችሏል
Aug 31, 2026 328
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን የሰላም ባለቤትነትና የጸጥታ ኃይሎችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማጠናከር ሰላምና ደኅንነት ይበልጥ ማረጋገጥ መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በየደረጃው ባሉ የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች ውይይት ተደርጎበት ዛሬ ይጠናቀቃል። በአምስት ዓመቱ ዕቅድ በከተማ ግብርና፣ በቤቶች ግንባታ፣ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በሌሎች ሰው ተኮር ሥራዎች የመዲናዋን ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ተግባራት ለማከናወን የሚያስችል የጋራ መግባባት ላይ ይደረሳል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተቋማት ያለፈውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሚገባ በመፈጸም ያሳዩትን ቁርጠኝነት በቀጣዮቹ ዓመታትም አጠናክረው እንዲቀጥሉ ግልጽና ሊያሰራ የሚችል ዕቅድ ነድፈው እንዲንቀሳቀሱ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የነዋሪዎችን የሰላም ባለቤትነትና የጸጥታ ኃይሎችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማጠናከር የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት ይበልጥ ማጠናከር ተችሏል። ሕዝቡን ያሳተፈ የጸጥታ ሥራ በማከናወን ሕገ ወጥ ተግባራትን የሚጠየፍ ማኅበረሰብ በመፍጠር መዲናዋ የሰላም ደሴት እንድትሆን ተደርጓል ብለዋል። አዲስ አበባ ዘላቂና አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ለማስቻል የመዲናዋ የሰላም ሠራዊት አደረጃጀት ገንቢ ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡን የሰላሙ ባለቤት በማድረግ ለእያንዳንዱ ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ ከጸጥታ ኃይሎች ጋር በቅንጅት የሚሰራበት አውድ ተፈጥሯል ብለዋል። ወንጀል ፈጽመው ለማምለጥ የሚሞክሩ ኃይሎችን በቀላሉ ለመቆጣጠር ከሸገር ሲቲ አስተዳደር ጋር በቅንጅት በመሥራት ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። በቀጣይም አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ አደራ በላቀ ደረጃ ለመፈጸም የሰላም፣ የጸጥታና ደህንነት ሥራ ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል። በዚህም የወንጀል ምጣኔን መቀነስ፣ የዜጎችን የሰላም ባለቤትነት ሚና ማላቅ፣ ልዩነቶችን በንግግር የሚፈታ ማኅበረሰብ በመፍጠር በሰላም እሴት ግንባታ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ሕገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ፣ የመሬት ወረራና ሕገ ወጥ ግንባታ እንዲሁም ሌሎች ወንጀሎችን በመቆጣጠር የሕግ የበላይነት የተረጋገጠባት መዲና የማድረግ ራዕይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የአፍሪካ የሰላምና ደኅንነት መዋቅር አስቸኳይ ማሻሻያ ያስፈልገዋል - መሐመድ አሊ የሱፍ
Aug 30, 2026 540
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ የሰላምና ደኅንነት መዋቅር በአስተማማኝ የገንዘብ ምንጭ የሚመራ አስቸኳይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐመድ አሊ የሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ኅብረት 21ኛውን አህጉራዊ ልዩ የግጭት መከላከልና አፈታት ጉባዔ በአንጎላ መዲና ሉዋንዳ አካሂዷል።   የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በጉባዔው ላይ እንዳሉት፤ የአፍሪካ የሰላምና ደኅንነት መዋቅር በአህጉሪቷ እየተደቀኑ ካሉ ሥጋቶች አኳያ አስቸኳይ ማሻሻያ ያስፈልገዋል። በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ እየታዩ የመጡት ቀጣይነት ያላቸው ቀውሶች የአህጉሪቷ ዋነኛ የሰላምና ደኅንነት ሥጋቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። ሽብርተኝነት፣ የጽንፈኝነት ጥቃት፣ የባሕር ላይ ዝርፊያ፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀልና ስደተኞችን አላግባብ ማስተናገድ የመሳሰሉ ሥጋቶች የአፍሪካ ሀገራት የጋራ እርምጃ እንዲወስዱ የሚጠይቁ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሊቀ መንበሩ ግጭትን መከላከል የኅብረቱ ቀዳሚ ትኩረት መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። የተጠናከረ አህጉራዊ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት፣ የኅብረቱ ውሳኔዎችን በተሻለ ሁኔታ መተግበርና ለሰላም ማስከበር ሥራዎች ዘላቂ የገንዘብ ምንጭ ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። ለዚህም በአስተማማኝ የገንዘብ ምንጭ የሚመራና የሚተዳደር የሰላም ፈንድ መኖሩ ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል።   ከተባበሩት መንግሥታት ጋር ያሉትን ጨምሮ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሽርክናዎች የአፍሪካን እውነታና ፍላጎት በሚያንጸባርቅ መልኩ መጠናከር እንዳለባቸውም ገልጸዋል። በተጨማሪም የኅብረቱ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማኅበረሰቦችና ቀጣናዊ ስልቶች በመከላከያ ዲፕሎማሲ ውስጥ ማዕከላዊ ሚና እንዳላቸው አጽንዖት ሰጥተዋል። በሰላምና ደኅንነት ምክር ቤት፣ በኮሚሽኑ፣ በአባል ሀገራትና በቀጣናዊ ተቋማት መካከል ቀጣይነት ያለው ምክክር ማድረግም ለጋራ ምላሽ አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል። የአፍሪካ የሰላምና ደኅንነት ሥጋቶችን አንድም ሀገር ብቻዋን መጋፈጥ እንደማትችል የሚያስገነዘቡ መሆናቸውን አብራርተዋል። ለዚህም የጋራ ሀብትን ማሰባሰብ፣ አጋርነትን ማጠናከርና በሰላምና ደኅንነት ጉዳይ የበለጠ የፓን-አፍሪካ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል። ሕገ-መንግሥታዊ ያልሆነ የመንግሥት ለውጥ የአፍሪካ ኅብረት አጥብቆ የሚኮንነውና በፅናት የሚቀጥል ግልጽ አቋም መሆኑን አንስተዋል። የኅብረቱ ልዩ ጉባዔም የአፍሪካን የሰላምና ደኅንነት ጉዳይ በጋራ በመረከብ የራሷን አቅም የምታጠናክርበት መድረክ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሊቀ መንበሩ በማጠቃለያ መልዕክታቸው፤ ይህ የረጅም ጊዜ ሥራ የማይታክት የፖለቲካ ቁርጠኝነትን የሚጠይቅ መሆኑን አስረድተዋል። ጉባዔው አፍሪካ የሰላምና ደኅንነቷን በጋራ በመረከብ የራሷን አቅም የምታጠናክርበት መፍትሔ አመላካች መድረክ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።    
ማህበራዊ
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ሁለንተናዊ ተቋማዊ የሪፎርም እርምጃ በአርዓያነት የሚወሰድ አስደናቂ ተግባር ነው
Aug 31, 2026 238
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25 /2018 (ኢዜአ)፦ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ አቅም የወሰደው ሁለንተናዊ ተቋማዊ የሪፎርም እርምጃ በአርዓያነት የሚወሰድ አስደናቂ ተግባር ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የአገልግሎቱ የለውጥ እርምጃዎች የሥራ ውጤታማነትን ከማላቅ እስከ ለምግብነት የሚውሉ የልማት ሥራዎች ተሰናስለው የተተገበሩበት መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጠይባ ሐሰን አስታውቀዋል።   የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ አቅም የወሰደውን ሁለንተናዊ ተቋማዊ የሪፎርም እርምጃ ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም በአገልግሎቱ ቅጥር ግቢ የተወሰዱ የተቋም ዕድሳት፣ በከተማ ግብርና የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የተከናወኑ የዶሮና በግ እርባታ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የንብ ማነብና ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸው የዕፅዋት ልማት ሥራዎችን አድንቀዋል። በጉብኝቱ ወቅትም የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ አቅም የወሰደው ሁለንተናዊ ተቋማዊ የሪፎርም እርምጃ በአርዓያነት የሚወሰድ አስደናቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።   የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጠይባ ሐሰን ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፤ በኢትዮጵያ በአብዛኛው ከጎረቤትና ከሌሎች ሀገሮች የመጡ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ዓለም አቀፍ ስደተኞችን በመቀበል፣ መብትና ክብራቸውን በማስጠበቅ ከተቀባዩ ማኅበረሰብ ጋር በማስተሣሠር በልማት ዕድሎች ተጠቃሚ እያደረገች ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ስደተኞችን የመቀበል ታሪካዊ እሴትም በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ፣ በውጭ ግንኙነትና በሀገር ገጽታ ግንባታ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የተቋሙን አገልግሎት ለማዘመን በራስ አቅም የተከናወኑ የሪፎርም እርምጃዎችም ለስደተኞችና ተገን ጠያቂዎች አገልግሎት የተሳለጠ የሥራ ከባቢ መፍጠር መቻሉን አንስተዋል። የአገልግሎቱ የሪፎርም እርምጃም ከዋና መሥሪያ ቤት እና በስድስት ክልሎች የሚገኙ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች እንዲሁም 25 መጠለያ ጣቢያዎች ድረስ የዘለቀ መሆኑን አስታውቀዋል። በተወሰዱ ተቋማዊ የሪፎርም እርምጃዎችም ከሕንፃ ዕድሳት ባሻገር በሰራተኛ አቅም ብቻ የተከናወኑ የዶሮና በግ እርባታ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የንብ ማነብና ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸው የዕፅዋት ልማት ሥራዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን አስረድተዋል። የተቋሙ የሪፎርምና የሌማት ትሩፋት የልማት ሥራዎችም ምቹና አረንጓዴ የሥራ ከባቢን በመፍጠር የራስን አቅም ለተሻለ ውጤት መጠቀም እንደሚቻል መልዕክት ያስተላለፈ ተምሳሌታዊ ተግባር ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም አገልግሎቱን ከኪራይ ቤት በማስወጣት ጭምር ዘመናዊ አገልግሎት መስጠትና ምቹ የሥራ ከባቢ መፈጠሩን አስታውሰዋል። ስደተኞችን በዲጂታል መታወቂያና በአገልግሎት መስጫ ምኅዳር ያለአንዳች መጨናነቅ በኦንላይን ቀጠሮ በውስን ደቂቃዎች ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጥበትን ምኅዳር በውስጥና በራስ አቅም መፍጠር እንደተቻለ አስረድተዋል።   የኢትዮጵያ ስደተኛ አያያዝ ታሪካዊና በየዘመኑ እየዘመነ የመጣ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅትም በሀገር ውስጥ እንደ ኢትዮጵያውያን እኩል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በቀጣይም በማካተት ፍኖተ ካርታ ትግበራ የበለጠ የመፈጸም አቅምን ለማጠናከር እንደሚሰራ በማስገንዘብ፣ ዓለም አቀፍ ልማት አጋሮችም የሚያደርጉትን ድጋፍ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ከአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጠይባ ሐሰንና የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በአገልግሎቱ ቅጥር ግቢ የአረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል።        
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ ዐቅም እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ኢትዮጵያ አካታች ልማት እያረጋገጠች መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው
Aug 31, 2026 279
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25 /2018 (ኢዜአ)፦የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ ዐቅም እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ኢትዮጵያ አካታች ልማት እያረጋገጠች መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ተገኝተው የተቋሙን የሪፎርም ስራዎች ተመልክተዋል። ከጉብኝቱ በኋላ ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የተከናወነው ሪፎርም የሥራ ቦታዎችን ከማሻሻል ባለፈ፣ የሥራ ባህልን፣ የአገልግሎት ጥራትንና ተቋማዊ ዐቅምን የሚያጎለብት አዎንታዊ ለውጥ መሆኑን ገልጸዋል።   የአገልግሎቱ አመራሮች፣ ሠራተኞችና ስደተኞች በመቀናጀት በዋና መሥሪያ ቤቱ፣ በ6 ክልሎች በሚገኙ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶችና በ27 መጠለያ ጣቢያዎች ያከናወኑት ሥራ በራስ ዐቅም ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ያሳየ ጥሩ ተሞክሮ መሆኑንም ጠቁመዋል። በተለይም የመደመር መንግሥት የግብርና እመርታ ማሳያ የሆነውን የሌማት ትሩፋት በመጠቀም በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በዶሮና እንስሳት እርባታ፣ በንብ ማነብና በተለያዩ የዕጽዋት ልማት ዘርፎች የተጀመሩ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህ ስኬት ተቋማዊ ሪፎርም የሚለካው በተሻለ የሥራ አካባቢ ብቻ ሳይሆን በሚፈጥረው ምርታማነትና ውጤት ጭምር መሆኑን ያረጋገጠ እንደሆነም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ዓለም አቀፍ ስደተኞችን በመቀበል፣ መብትና ክብራቸውን በማስጠበቅ እንዲሁም ከተቀባዩ ማኅበረሰብ ጋር በማስተሣሠር በልማት ዕድሎች ተጠቃሚ እያደረገች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።   አክለውም ስደተኞቹ የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ መሆናቸው ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፏቸውን በእጅጉ እያሳደገው ይገኛል ብለዋል። በራስ ዐቅም የሚመጣ ለውጥ የተቋምን ዐቅም እንደሚያጎለብትና ይህም የሀገርን ዐቅም እንደሚገነባ ጠቁመው፤ በስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት የታየው ስኬታማ ጉዞ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጤና አገልግሎት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች ተመዝግበዋል
Aug 31, 2026 235
​ወልቂጤ፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጤና አገልግሎቱን ለማጠናከር በተከናወኑ ተግባራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች መመዝገባቸው የክልሉ የጤና ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ጤና ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ላይ በወልቂጤ ከተማ ውይይት አካሂዷል። የቢሮው ሃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በዚህ ወቅት እንዳሉት የጤናውን ዘርፍ ለማዘመን በተደረገ ጥረት ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ውጤታማ የሕክምና አገልግሎት መስጠት ተችሏል።   ይህም በወሊድ ወቅት የሚከሰቱ የእናቶችና የሕጻናት ሞትን በመቀነስ የእናቶችን በጤና ተቋማት የመውለድ ምጣኔ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። ​በህብረተሰብ አቀፍ የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም አማካኝነትም ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫና የመከላከያ ሥራዎች በመሰራቱ የተላላፊ በሽታዎች ስርጭት በከፍተኛ ደረጃ ቀንሷል ብለዋል። ህብረተሰቡን በማሳተፍ ወባማ በሆኑ አካባቢዎች የትንኝ መራቢያ ስፍራዎችን ከማፋሰስና ከማዳፈን ባለፈ የአጎበር አጠቃቀምን ለማሳደግ መቻሉንም ተናግረዋል። በእዚህም በክልሉ የወባ በሽታ በወረርሽኝ መልክ እንዳይከሰት ለመከላከል ተችሏል ብለዋል። በጤና ተቋማት መድኃኒትና የሕክምና መገልገያ ቁሶችን በማሟላትና የአገልግሎት ጥራትን በማሻሻል ረገድ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውንም አቶ ሳሙኤል አክለው ገልጸዋል።   ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ በተከናወኑ ሥራዎችም ተጨባጭ ለውጦች መምጣታቸውን ነው ያስታወቁት። የጤና ባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ​የሕጻናትና የእናቶች ጤና አገልግሎት ሽፋንና ጥራት ለማሳደግ በልዩ ትኩረት በመሰራቱ በጤና ተቋም የማይወልዱ እናቶች የማይገኙባቸውን ቀበሌዎቸ ተፈጥረዋል ብለዋል። ለሁለት ቀናት እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የክልሉ ጤና ቢሮ አመራሮች፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ፣ የሆስፒታልና የጤና ጣቢያ ሥራ ሃላፊዎች በመሳትፍ ላይ ናቸው።  
ባህላዊ ጥበብ ለኢኮኖሚ እድገት- የእደ-ጥበብ ውጤቶች በሐረሪ ክልል
Aug 31, 2026 205
በሐረሪ ክልል ባለፉት ዓመታት የእደጥበብ ውጤቶች እንዲዳብሩና የህዝብ ተጠቃሚነት የበለጠ እንዲጎለብቱ በማስቻል ረገድ ስኬታማ ስራዎች ተከናውነዋል። የሀረሪ ክልል መንግሥት የቱሪዝም ዘርፉን የዕድገትና ብልፅግና መሠረቶች መካከል አንዱ በማድረግ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። በተለይም የሐረሪ ሕዝብ እደ ጥበብ ውጤት የሆነው እና በክልሉ በሰፊው የሚመረተው የሐረር የጌይ ሞኦት (አለላ ስፌት) ምርት በዓለም አቀፍ ምድብ የንግድ ምልክት (ብራንድ) ሆኖ መመዝገቡ የዘርፉ አንዱ ማሳያ ሆኗል። ​ይህ ታላቅ ምዕራፍ የአዕምሮአዊ ንብረት ባለቤትነትን ለማስጠበቅ እና የዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎን ለማዳበር ከፍተኛ ፋይዳ አለው።   የአለላ ስፌት ምርት በዓለም አቀፍ ምድብ የንግድ ምልክት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማግኘቱ፤ ለቱሪዝም ዘርፍ ልማት እና በዘርፉ ለተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ትልቅ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን የሚያስገኝ ነው። ​በእያንዳንዱ የሐረሪ ቤት ባህላዊ የአለላ ስፌት ምርቶች መኖራቸው ከስጦታ፣ ከቤት ውስጥ መገልገያነትና ከማስዋቢያነት አገልግሎታቸው ባሻገር የማንነትና የባህል የላቀ መገለጫ በመሆናቸው ጭምር ነው። እነዚህ የእደ-ጥበብ ውጤቶች በዓለም አቀፍ ገበያ የብራንድ እውቅና ማግኘታቸው የሐረርን ባህል፣ እሴትና ማንነት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ ትልቅ በር የሚከፍት ነው። ​ይህም በሥራው የሚሳተፉ ዜጎች በአገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ገበያ የመሳተፍና ተጠቃሚ የመሆን እድላቸውን በእጅጉ እንደሚያሰፋውና የክልሉን የቱሪዝም ዘርፍ ገቢ ከፍ ከማድረግ አንፃር የጎላ ሚና ይጫወታል።   ​የመደመር መንግሥት ቅርሶቻችን የሀገር ኩራት እንዲሆኑ እና እደ-ጥበብ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን ሚና ይበልጥ ለማጎልበት የጀመረውን ሁለገብ ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል።
ኢኮኖሚ
በአማራ ክልል የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ አበረታች ውጤት እያስመዘገበ ነው
Sep 1, 2026 25
ጎንደር፤ ነሐሴ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እና የሥርዓተ-ምግብ ችግርን በመቅረፍ ረገድ አበረታች ውጤት ማስገኘቱን የአማራ ክልል እንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ያለበትን ደረጃ እና በምርት አቅርቦት ረገድ እያስገኘ ያለውን ውጤት በጎንደር ከተማ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሁነኛው በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የሥርዓተ-ምግብን ለማሻሻል የሌማት ትሩፋትን በስፋት የመተግበር ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። መርሃ ግብሩ በቂ ምርት ለማቅረብ፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የሚያስችል ውጤት ማስገኘቱንም ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የበጀት ዓመትም ከ1 ነጥብ 6 ቢሊየን በላይ እንቁላል፣ ከሁለት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ቶን በላይ ወተት እና 900 ሺህ ቶን የሥጋ ምርት በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን በማሳያነት አንስተዋል። በተጨማሪም ከ36 ሺህ ቶን በላይ ማር በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ጠቁመው፤ የዓሣ ልማቱንም በሐይቆች፣ በወንዞች እና በሰው ሠራሽ ኩሬዎች ጭምር በማስፋት አበረታች ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል። ለሌማት ትሩፋት ማነቆ የነበረውን የመኖ እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍም 46 ዘመናዊ የመኖ ማቀናበሪያ ፋብሪካዎችን ወደ ማምረት ማስገባት መቻሉንም ጠቅሰዋል። በከተሞችና አካባቢው በስፋት እየተካሄደ የሚገኘውን የሌማት ትሩፋት በቀጣይም በሁሉም የገጠር አካባቢዎች ለማስፋት የልምድ ልውውጥ እየተደረገ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። በጎንደር ከተማ አስተዳደር እንስሳትና ዓሣ ሀብት መምሪያ የኤክስቴንሽን ኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ ሀብታሙ ዘገዬ ፤ ተግባራዊ የተደረገው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በየዘርፉ ውጤት ተገኝቶበታል ብለዋል። በዘርፉ ተደራጅተው ወደ ሥራ ለገቡ ወጣቶች የብድር፣ የቦታ እና ሌሎች ድጋፎችን በመስጠት የከተማውን የእንቁላል፣ የወተትና የሥጋ አቅርቦት እጥረት በአጭር ጊዜ ማሻሻል መቻሉን አስረድተዋል። ለመጪው የአዲስ ዓመት በዓልም ከ65 ሺህ በላይ የሥጋ ዶሮ፣ 40 ሺህ የደለበ በግና ፍየል በማቅረብ ገበያውን ለማረጋጋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል። በከተማው በዶሮና ንብ እርባታ የተሰማሩት ወይዘሮ ፅላተማርያም ተመስገን እንደተናገሩት፤ በ50 ጫጩቶች የጀመሩት የዶሮ እርባታ ሥራ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓትም በሦስት ቅርንጫፎች 47 ሺህ እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማራባት በቀን እስከ 27 ሺህ የሚደርስ እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ ባደረገላቸው ድጋፍ የንብና የዓሣ ልማትን በተቀናጀ አግባብ መጀመራቸውን አመልክተው፤ በተሰማሩበት መስክም ለ137 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም ተናግረዋል። የ"ዘርፌ፣ ሀና እና ጓደኞቻቸው" ሽርክና ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሽመልስ አርጋው በበኩላቸው፤ በ45 ሺህ ብር የጀመሩትን የወተት ልማት ስራ ላይ ጠንክረው በመሥራት ውጤታማ መሆን መቻላቸውን አመልክተዋል።
አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የመዲናዋ የአመራር አባላት በቁርጠኝነት ሊተጉ ይገባል
Aug 31, 2026 286
አዲስ አበባ ፣ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የመዲናዋ የአመራር አባላት በቁርጠኝነት ሊተጉ እንደሚገባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት እና በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ላለፉት ሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ውይይት አጠናቋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በውይይቱ ማጠቃለያ ባስተላለፉት የሥራ መመሪያ፤ መዲናዋን የብልጽግና ተምሳሌት የሚያደርጉ ተጨባጭ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተሻለ አቅም የመፈጸም ልምድ እየጎለበተ መሆኑን ገልጸው፤ በውጤታማ የሀብት አጠቃቀም የተመደበው ገንዘብ ለታለመለት ዓላማ በማዋል የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል ብለዋል። የሙሉ ቀን ሥራ ባህል እየሆነ መምጣቱን በማንሳት፤ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመለወጥ ዜጎቸን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ገቢራዊ በማድረግ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋለውን የመልካም አስተዳደር ችግር በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል ውጤት ተገኝቷል ብለዋል። በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ በመንገድ፣ በጤና፣ ትምህርት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ በወንዝ ዳርቻዎችና ኮሪደር ልማት ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎቸን ለማከናወን ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል። በመሆኑም አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የመዲናዋ የአመራር አባላት በቁርጠኝነት ሊተጉ ይገባል ብለዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጃንጥራር ዓባይ በበኩላቸው፤ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት የአመራር አባላት የጋራ ግንዛቤ በመያዝ የለውጥ ርምጃዎችን መጀመር እንዳለባቸው ገልጸዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ዲሞክራሲ ስርዓት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ እንዳሉት፣ህዝቡ በምርጫው የሰጠንን ተጨማሪ ዕድል በልማት ለመካስ ለቀጣይ ተልዕኮ ራሳችንን ማዘጋጀት ይገባናል ብለዋል።
በአማራ ክልል ከአምስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ተሸፍኗል
Aug 31, 2026 103
ባህርዳር፣ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል በተያዘው የመኸር ወቅት የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ከአምስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈን መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ። የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማደፍሮ አስላከ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በ2018/19 የምርት ዘመን በምግብ ራስን ከመቻል ያለፈ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት እየተሰራ ነው። በምርት ዘመኑ ከአምስት ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በማልማት የእንክብካቤ ስራ ማከናወን እየተካሄደ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   አጠቃላይ ከለማው መሬት ውስጥ ከአንድ ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘመናዊ ትራክተር በማረስ ማልማት መቻሉንም አመልክተዋል። ከሶስት ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ሄክታር በላይ የሚሆነውን መሬት ደግሞ በኩታ ገጠም የአስተራረስ ዘዴ የለማ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም አርሶ አደሩ ሰብሉን የማረም፣ የመኮትኮትና ከተባይና ከበሽታ በመከላከል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ለዚህ የምርት ዘመንም አምስት ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ዘመናዊ የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ 524 ሺህ ኩንታል የተለያየ ምርጥ ዘር ጥቅም ላይ መዋሉን አስገንዝበዋል። በአሁኑ ወቅት ያለው አፈጻጸም በምርት ዘመኑ ይገኛል ተብሎ የታቀደውን ከ205 ሚሊዮን ኩንታል በላይ አጠቃላይ ምርት ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን የወንበርማ ወረዳ አርሶ አደር ቸኮል ታደለ፤ አራት ሄክታር መሬታቸውን በኩታ ገጠም አስተራረስና በትራክተር በማረስ በቆሎና ስንዴ መዝራታቸውን ገልጸዋል። በባለሙያዎች ምክረ ሃሳብ በመታገዝ የማዳበሪያና የምርጥ ዘር ግብዓት ተጠቅመው ያለሙት ሰብል እድገቱና ቁመናው በተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከሁለት ሄክታር በላይ መሬታቸውን በወቅቱ በዘር ሸፍነው እየተንከባከቡ እንደሚገኙ የገለጹት ደግሞ በሰሜን ጎጃም ዞን የጎንጅ ቆለላ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አለምነው ደሴ ናቸው። እያለሙት ያለው ጤፍና የበቆሎ ሰብል በጥሩ ቁመና ላይ የሚገኝ በመሆኑ የተሻለ ምርት አገኛለሁ ብለው እየሰሩ መሆናቸውን ነው የጠቀሱት። በ2017/2018 የምርት ዘመን በክልሉ ከለማው አምስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ከ188 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማምረት መቻሉን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።  
ሕብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ልምዱን በማሳደግ አምራቹን ማበረታታት አለበት - ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Aug 31, 2026 96
ሃዋሳ፤ ነሐሴ 25/2018(ኢዜአ)፡-ሕብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ልምዱን በማሳዳግ በአምራች ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶችን ማበረታታት እንዳለበት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ አስታወቁ። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ''የኢትዮጵያን ይግዙ'' በሚል መሪ ሃሳብ በሀዋሳ ከተማ የተዘጋጀውን የንግድ አውደ ርዕይና ባዛር ከፈተዋል።   በንግድ አውደ ርዕዩና ባዛሩ የቀረቡ ምርቶችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ርዕሰ መስተዳድሩ ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ባህሉን እንዲያሳድግ ጠይቀዋል። የንግድ ሳምንቱ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተረጋጋ የግብይት ሥርዓት እንዲፈጠር አጋዥ መሆኑንም ገልጸዋል። ማህበረሰቡ በአምራች ኢንዱስትሪ መስክ የተሰማሩ ባለሀብቶችን ለማገዝና የሀገር ኢኮኖሚን ለመደገፍ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመግዛትና የመጠቀም ልምዱን ማጎልበት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሃላፊዋ ወይዘሮ ሰላማዊት መኩሪያ በበኩላቸው እንዳሉት አውደ ርዕይና ባዛሩ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ባህልን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ አቅምን ለማጠናከር ያለመ ነው፡፡ በአውደ ርዕዩና ባዛሩ ላይ ቁጥራቸው 168 የሚሆኑ አምራቾች፣ ነጋዴዎች፣ ዩኒየኖች፣ ላኪዎች፣ አገልግሎት ሰጪዎችና በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ላይ የሚሳተፉ ማህበራት ጭምር መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡   በዚህም መጪዎቹን በዓላት ታሳቢ ያደረጉ የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያን የማረጋጋት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አውደ ርዕይና ባዛሩ ዘላቂ የገበያ ትስስር በመፍጠር በኢኮኖሚ እንቅስቃሴው ላይ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በአውደ ርዕይና ባዛሩ ላይ ምርታቸውን ካቀረቡት መካከል የሲዳማ ዶና ህብረት ሥራ ዩኒየን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ገነነ ልኡልሰገድ የአትክልና ፍራፍሬ ምርቶችን ይዘው መቅረባቸውን ገልጸዋል። ከ5ሺህ በላይ አባላት የሚሰበስቧቸውን ምርቶችን በተሻለ የገበያ አማራጭ በማቅረብ ገበያን ከማረጋጋት ባለፈ የአባላቱን የገቢ አቅም እያሳደጉ መሆኑን ገልጸዋል። "የኢትዮጵያን ይግዙ" የንግድ አውደ ርዕይና ባዛር የገበያ ትስስር የሚፈጥር ምቹ አጋጣሚ በመሆኑ የአካባቢውን ምርት በሚገባ ለማስተዋወቅ እንደሚጠቀሙበት ገልጸዋል። የብራውን ፉድ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ተወካይ አቶ መርዕድ ጋሹ የንግድ አውደ ርዕይና ባዛሩ ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ የተሻለ የገበያ ትስስር እንደሚፈጥሩበት ገልጸዋል። የንግድ አውደ ርዕዩና ባዘሩ እስከ ጳጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚቆይ በስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚጠይቀውን የዲጂታል ክህሎት የታጠቀ ትውልድ ማፍራት እያስቻለ ነው - አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ
Aug 30, 2026 348
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በኢትዮ-ኮደርስ የአምስት ሚሊየን ስልጠና መርሃ ግብር በዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የበለፀገ የሰው ሃይል ለማፍራት በትኩረት እንደሚሰራ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በየደረጃው ባሉ የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች ውይይት እየተደረገበት ነው።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት ባለፉት አምስት ዓመት በስትራቴጂክ ዕቅድ የመፈጸም ቁርጠኝነታቸውን በቀጣዮቹ ዓመታትም አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የወጣቶችን ተሳትፎና ፈጠራ ማበረታታት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ባለፉት አምስት ዓመታትም ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የመዲናዋ ዜጎችን የሥራ ዕድል በመፍጠር የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደተቻለ ገልጸዋል። በዚህም የአዲስ አበባ ወጣቶች በግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ኮንስትራክሽን፣ አገልግሎትናበሌሎች ዘርፎች ተጠቃሚ የሚሆኑበት ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። በቀጣይም የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አጫጭርና መካከለኛ ሥልጠና በመስጠት ለኢንተርፕራይዞች በቂ የገንዘብ ብድር አቅርቦት እንደሚመቻች አስረድተዋል። የአዲስ አበባን የዓለም የዲፕሎማሲ ከተማነት የሚመጥንና ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ልህቀት የታጠቀ ወጣት የሰው ሃይል ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የኢትዮ-ኮደርስ የአምስት ሚሊዮን ስልጠና መርሃ ግብር ይፋ በተደረገ ማግስት ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ወጣቶች የሥልጠናው ተካፋይ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታትም ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የመዲናዋ ዜጎች ስልጠና በመስጠት በየትኛውም የዓለም ጫፍ የበይነ መረብ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። በዚህም የ21ኛው ክፍለ ዘመን የቴክኖሎጂና ዲጂታል ሥምሪት የሚጠይቀውን ዕውቀትና ክህሎት የተላበሰ ወጣት ለማፍራት የኮደርስ ሥልጠና ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ደሳለኝ ተረፈ በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ አንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በተቋቋመ ማግስት የተገልጋዮችን እርካታ ከ99 በመቶ በላይ ማድረስ አስችሏል ብለዋል። በመዲናዋ በ11 ማዕከላት 25 የአዲስ አበባና የፌዴራል ተቋማት 150 አገልግሎቶችን እየሰጡ መሆኑን ገልጸው፤ እስከ መስከረም ወር ተጨማሪ ማዕከላት ይገነባሉ ብለዋል። በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የአገልግሎት አሰጣጡን ከእርካታ ወደ አመኔታ የማሸጋገር ዕቅድ መያዙን በማንሳት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን በተለያዩ አማራጮች እንደሚሰጥ ገልጸዋል።  
የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ማደግና ዲጂታላይዜሽን የዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ እያሻሻለ ነው
Aug 29, 2026 171
ቦንጋ ፤ ነሐሴ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ማደግና ዲጂታላይዜሽን የዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ እያሻሻለ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የቦንጋ ከተማ ነዋሪ ምሁራን ገለጹ። የመደመር መንግሥት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ለማፋጠንና አገልግሎቶችን ለማዘመን የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን በተግባር ማየታቸውንም ምሁራኑ ተናግረዋል። የኮሌጁ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምህር ምስጋናው ታደሰ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የዲጂታላይዜሽን ትግበራ የሀገር ልማትን ፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን፣ የመንግሥት አሠራር ብቃትን ማሳደጊያ እና የዜጎችን ኑሮ ማሻሻያ መሣሪያ ነው። የመደመር መንግሥት ለዲጂታላይዜሽን በሰጠው ልዩ ትኩረት ውስጥ ተግባራዊ የተደረገው የዲጂታል 2025 እስትራቴጂ የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ በተጨባጭ ማሻሻሉንም ነው ምሁሩ የተናገሩት። በዚህ እስትራቴጂ በሞባይል ባንኪንግ፣ በቴሌኮሙኒኬሽን፣ በኦንላይን አገልግሎቶችና በዲጂታል መታወቂያ ዘርፎች የተመዘገቡ ለውጦች ዜጎች የተለያዩ አገልግሎቶችን በቀላሉና በተፋጠነ መንገድ እንዲያገኙ ያደረጉ መሆኑን አንስተዋል። በኢኮኖሚው ዘርፍም አዳዲስ የንግድ ዕድሎችን የፈጠረ ሲሆን የዚሁ አካል የሆነው የ‘ኢትዮ-ኮደርስ’ ፕሮግራም ወጣቶችን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ከመሆን ባለፈ የቴክኖሎጂ ፈጣሪ እንዲሆኑ ትልቅ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። በመሆኑም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተገኙ አበረታች ውጤቶች ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ጠንካራ መሠረት የጣሉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት በዘርፉ የተከናወኑት ተግባራት ዲጂታል ኢኮኖሚውን በማስፋፋት የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሻሻላቸውን የገለጹት ደግሞ የኮሌጁ የመረጃ ቴክኖሎጂ መምህር ታደሰ ዘውዴ ናቸው። ከዚህ ውስጥም የ‘መሶብ’ የአንድ ማዕከል አሠራር የመንግሥት አገልግሎቶችን ተደራሽነት በማሻሻል ዜጎች ጊዜና ወጪያቸውን በቆጠበ መልኩ የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ያደረገ መሆኑንም ለአብነት አንስተዋል። የዲጂታል 2025 መጠናቀቅን ተከትሎ የተተገበረው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በኢኮኖሚው ዘርፍና በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰፊ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑንም ነው የገለጹት።
በአማራ ክልል የመሶብ አንድ ማዕከልን ጨምሮ ከ35 በላይ የዲጂታል አሰራሮችን ለመዘርጋት ተችሏል- ቢሮው
Aug 28, 2026 156
ባህር ዳር፡ ነሐሴ 22/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የመሶብ አንድ ማዕከልን ጨምሮ ከ35 በላይ የዲጂታል አሰራሮችን በመዘርጋት ቀልጣፋና ከብልሹ አሰራር የጸዳ አገልግሎት መስጠት መቻሉን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ የቻለ ይግዛው ባለፉት ሦስት ዓመታት በዲጂታላይዜሽን ትግበራ በተመዘገቡ ውጤቶችና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ዛሬመግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የመሶብ አንድ ማዕከላትን ጨምሮ የተለያዩ ዘመናዊ መተግበሪያዎችን በማልማት ለህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ተችሏል። የክልሉ መንግሥት በ25 ዓመት የስትራቴጂክና አሻጋሪ ዕቅዱ ለቴክኖሎጂው ዘርፍ በሰጠው ትኩረት መሠረት፣ አገልግሎት በሚበዛባቸው ተቋማት ላይ በማተኮር ከ35 በላይ የዲጂታል አሰራሮች መዘርጋቱን ነው የገለጹት። ቴክኖሎጂዎቹ በፍትሕ ሥርዓት፣ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም፣ ኢንቨስትመንት በመሳብና በግብርናው ዘርፍ ላይ አዎንታዊ ለውጥ እንዲመጣ ማስቻላቸውንም አብራርተዋል። በተጨማሪም ቴክኖሎጂዎቹ የመንግሥት አካላት በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ እንዲሰጡ ከማድረጋቸው ባሻገር፣ ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን ለማስወገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን አስረድተዋል። በተለይም "መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በክልል ደረጃ በባህር ዳር፣ ደሴና ወልዲያ ከተሞች ተግባራዊ በማድረግ የህዝቡን እርካታ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። በተካሄደው የዳሰሳ ጥናትም እስካሁን ከ103 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በኩል ፈጣን ፣ ፍትሐዊና ከብልሹ አሰራር የጸዳ አገልግሎት ማግኘታቸው መረጋገጡን አስገንዝበዋል። በአሁኑ ወቅትም የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን ወደ ሌሎች ከተሞች ለማስፋት የግንባታና የቴክኖሎጂ ዝርጋታ ሥራው እየተፋጠነ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በቀጣይ ዓመትም የዲጂታል 2030ን ግብ ለማሳካት ተጨማሪ ከ13 በላይ አዳዲስ መተግበሪያዎችን የማልማት ስራ እንደሚከናወን አብራርተዋል። በክልሉ በዲጂታል ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትን ለህዝብ ለማስተዋወቅ ያለመ የፓናል ውይይትና የኤግዚቢሽን መርሃ-ግብር ከነሐሴ 28 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ እንደሚካሄድ ተመላክቷል።  
የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባዔ ኢትዮጵያ በክትባትና በጤና ምርምር ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ውጤቶች ለማስተዋወቅ ምቹ አጋጣሚ ፈጥሯል
Aug 28, 2026 227
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባዔ ኢትዮጵያ በክትባትና በጤና ምርምር ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ውጤታማ ተግባራት ለማስተዋወቅ ምቹ አጋጣሚ መፍጠሩን የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ገለጹ። በአዲስ አበባ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ኮሚቴ ጉባዔ በትናንትናው ዕለት በስኬት መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡ የጉባዔው ተሳታፊዎች በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የሚገኘውን የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩትን በመጎብኘት በሥራ ላይ ያሉ አቅሞችንና የምርምር ሥራዎችን ተመልክተዋል፡፡   የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በጉባዔው በጤና ምርምር ዘርፎች ያስመዘገበቻቸውን ውጤታማ ተግባራት ለአህጉሩ ተወካዮች ማጋራት ችላለች፡፡ በመድረኩ በጤና መረጃ ሥርዓት ትንተና፣ በአቅም ግንባታ እና በክትባት ዙሪያ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች አጋርታለች ብለዋል፡፡ ተጨባጭ ስኬቶቿን እንድታሳይ ከማስቻሉም በላይ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የጠበቀ የላቦራቶሪና የምርምር ትስስር እንድትፈጥር ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ የጋራ ልምድ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል መፍጠሩንም እንዲሁ፡፡ በጉባዔው ወቅት የቀረቡት የምርምርና የአቅም ግንባታ ሥርዓቶች በቀጣይ ለሚከናወኑ ሀገራዊና አህጉራዊ የጤና ሥራዎች በበጎ መነሻነት የሚያገለግሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ጉባዔው ለኢትዮጵያም ሆነ ለተሳታፊ ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ መልካም አጋጣሚ እንደነበር አብራርተዋል፡፡   በጋምቢያ የጤና ሚኒስቴር የጤና አገልግሎት ዳይሬክተር (ዶ/ር) ሞሞዶ ንያሲ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ የጤና ሥርዓት ሂደቱ እጅግ ፈጣንና በትክክለኛው አቅጣጫ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ በተለይ የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ለአጠቃላይ የአፍሪካ አህጉር የሚመጥን ትልቅ የልህቀት ማዕከል መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የህክምና ባለሙያዎቻቸውንና ተመራማሪዎቻቸውን ለልምድ ልውውጥ፣ ለምርምር፣ ለፈጠራ ሥራዎችና ለትምህርት ሊልኩበት የሚችሉበት ተስፋ ሰጪ ኢንስቲትዩት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካን የጤና አጀንዳ በተሻለ ደረጃ ለማሳካትና አህጉራዊ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ከኢንስቲትዩቱ ጋር የጠበቀና የተቀናጀ የትብብር ግንኙነት ለመሥራት በጉጉት እንደሚጠብቁም ተናግረዋል፡፡
ስፖርት
አርሰናል ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ
Sep 1, 2026 139
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል አስቶንቪላ 1 ለ ዐ አሸንፏል። ማምሻውን በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቡካዮ ሳካ በ59ኛው ደቂቃ ግቧን አስቆጥሯል። የ24 ዓመቱ የክንፍ መስመር ተጫዋች በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እምብዛም ግልጽ የግብ እድሎች ባልተፈጠሩበት ጨዋታ አርሰናል ያገኘውን የግብ እድል በሚገባ ተጠቅሟል። አስቶንቪላ ወደ አርሰናል የግብ ክልል በተደጋጋሚ ጊዜ ቢደርስም ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ማድረግ ተስኖታል። በ75 ሚሊዮን ፓውንድ ከኒውካስትል ዩናይትድ ወደ አርሰናል የተዘዋወረው ብሩኖ ጉማራይሽ ተቀይሮ በመግባት የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ተከታታይ ድሉን አግኝቷል። በአንጻሩ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት በርካታ ቁልፍ ተጫዋቾቹን ያጣው አስቶንቪላ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል። አስቶንቪላ በሁለቱ የሊግ ጨዋታዎች ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ማድረግ አልቻለም። በሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶንቪላ ከአዲስ አዳጊው ሁል ሲቲ ጋር ይጫወታል። በለንደን ደርቢ አርሰናል ከቼልሲ የሚያደርገው ጨዋታ ከወዲሁ ተጠባቂ ነው። የሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳሉ።
አርጀንቲናው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ከብሔራዊ ቡድኑ ራሱን አገለለ
Aug 31, 2026 103
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2018 (ኢዜአ)፦ የ39 ዓመቱ ሊዮኔል ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ራሱን ማግለሉን ይፋ አድርጓል። ሜሲ በኢንስታግራም ገጹ ባሰፈረው መልዕክት ከፍጻሜው ጨዋታ አንስቶ ነገሮችን በጥልቀት ካሰብኩ በኋላ፣ ከብሔራዊ ቡድን ራሴን ማግለሌን ለሁሉም ማሳወቅ እፈልጋለሁ ሲል ተናግሯል። ውሳኔው ውስጤን ቢጎዳውም እና በጣም ስሜታዊ የሚያደርገኝ ቢሆንም ራሴን የማግለሉ ጊዜ አሁን ነው ብሏል። የአርጀንቲናን ማልያ ለብሼ የምችለውን ሁሉ አድርጊያሁ፣ አርጀንቲናዊ በመሆናችሁ ኩራት እንዲሰማችሁ ለማድረግም ሁሉንም ነገር ሰጥቻለሁ ብሏል። ሜሲ አያይዞም የብሔራዊ ቡድን ቆይታው ሁልጊዜ በልቡ እንደሚኖር ገልጾ፣ አሁን ላይ አዲስ እና ወጣት ተጫዋቾች ዕድሉን ማግኘት እንዳለባቸው አንስቷል። ይህንን የስንብት ጽሑፍ የጻፈው ከዓለም ዋንጫው ፍጻሜ ጨዋታ ከሁለት ቀናት በኋላ እንደነበር ገልጾ፣ ከአባቱ ሞት በኋላ እያሳለፈው ያለው ጊዜ ዛሬ ላይ ውሳኔውን እንዲያሳልፍ እንዳስገደደው አመልክቷል። በእነዚህ 20 ዓመታት ውስጥ አርጀንቲናውያን ላሳዩት ፍቅር ምስጋና ያቀረበ ሲሆን ከብሔራዊ ቡድኑ ጎን በመልካምም በክፉም ጊዜ እንደሚቆም ተናግሯል። የሜሲ ውሳኔ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያ ሆኗል። ሊዮኔል ሜሲ ከእ.አ.አ ከ2005 እስከ 2026 በአርጀንቲና ማልያ ባደረጋቸው 207 ጨዋታዎችን 125 ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የምንጊዜም የሀገሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኗል። በአርጀንቲና ማልያ 65 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል። በቅርቡ በተካሄደው 23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ስምንት ጎሎችን ያስቆጠረ ሲሆን በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ 22 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ከፈረንሳዊው ኪሊያን ምባፔ (23 ጎሎች) በመቀጠል በዓለም ዋንጫው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ደረጃ ዝርዝር ውስጥ ተቀምጧል። ሊዮኔል ሜሲ በታሪኩ በአጠቃላይ 46 ዋንጫዎችን በማንሳት በእግር ኳስ ታሪክ ከፍተኛውን የዋንጫ ብዛት የሰበሰበ ባለክረብ-ወሰን ተጫዋች ነው። ሊዮኔል ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ጋር በአጠቃላይ የተለያዩ ዋንጫዎችን አንስቷል። የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፣ ሁለት የኮፓ አሜሪካ ዋንጫዎች፣ የአውሮፓ እና ደቡብ አሜሪካ ሻምፒዮናዎችን ያገናኘው የፋይናሊሲማ ዋንጫ፣ እንዲሁም የኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ እና ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ክብርን ተጎናጽፏል። ሊዮኔል ሜሲ በአሁኑ ሰዓት ለአሜሪካው ኢንተር ሚያሚ ክለብ እየተጫወተ ይገኛል።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ቃል ኪዳን
Sep 1, 2026 87
የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎች በአፍሪካ ላይ ማረፍ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከተከታታይ የድርቅ ክስተቶች እስከ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋዎች አህጉሪቷን በከፍተኛ ሁኔታ እየተፈታተኑም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በእነዚህና በሌሎች ፈተናዎች ውስጥ የአፍሪካ አረንጓዴ ትራንስፎርሜሽን ግንባር ቀደም ተዋናይ ሆና መጥታለች። በዚህም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎችን ከወረቀት አልፎ በተግባር በመከወን ስኬታማና ተጨባጭ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። እ.አ.አ በ2011 ይፋ የሆነው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ከኢኮኖሚ እድገት ጎን ለጎን ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር እና ከካርቦን ነጻ የሆነ ኢኮኖሚን የመገንባት ውጥን ያለው ነው። ስትራቴጂውም አራት አንኳር ምሰሶዎች አሉት፦ የመጀመሪያው ዘላቂ ግብርና እና የቁም እንስሳት ውጤታማነትን ማሳደግ ሲሆን በዚህ ውስጥ ምርታማነትንና የአርሶ አደሮችን ገቢ መጨመር እንዲሁም የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ብክለትን መቀነስ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በደን ልማት አማካኝነት ለደኖች ጥበቃ ማድረግ፣ የደን መልሶ ልማት እና ካርቦንን አምቆ መያዝ የሚያስችሉ ግዙፍ አረንጓዴ ፕሮጀክቶችን ወደ ትግበራ ማስገባት ሁለተኛው ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ነው። የሃይድሮ፣ የእንፋሎት፣ የንፋስ እና የፀሐይ ታዳሽ ኃይሎችን ማስፋፋት ሌላኛው የትኩረት ማዕከል መሆኑ በስትራቴጂክ ሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በትራንስፖርት፣ በኢንዱስትሪና በመሰረተ ልማት ግንባታዎች ዘመናዊ እና ኃይል ቆጣቢ የቴክኖሎጂ አማራጮችን መጠቀም አራተኛው ጉዳይ ነው። አረንጓዴ አሻራ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ትልቁ የተግባር ማሳያ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ እስከ አሁን ከ54 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። የአካባቢ ጥበቃ ስራ ማህበረሰብን በግልጽ በማሳተፍ በመተግበር ላይ የሚገኝ ትልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው። ኢትዮጵያ የኃይል ምንጭ አማራጮቿን ከታዳሽ ኃይል እያገኘች መሆኗም የስትራቴጂውን ስኬታማነት ያመላክታል። ብዝኃ የኢነርጂ አማራጮችን መጠቀም ከብክለት ነጻ የኃይል አቅርቦት እንዲገኝ እያደረገ ነው። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ትውልድን የሚሻገር ሁሉን አቀፍ እሳቤ ሲሆን፤ ስትራቴጂው የኢኮኖሚ እድገትን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ያስተሳሰረና የብክለት ቅነሳን የሚያረጋግጥም ነው። በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን ከመትከል እስከ የታዳሽ የኃይል ምንጭን ማስፋት የኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት እመርታ በተግባር ገልጣ ማሳየት እያስቻላትም ይገኛል።
የሀዋሳ ከተማን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚመጥኑ ውጤታማ የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ -ከንቲባ ጥራቱ በየነ
Aug 29, 2026 160
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የሀዋሳ ከተማን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚመጥኑ ውጤታማ የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለፁ። በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ጽህፈት ቤት "ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" በሚል መሪ ሀሳብ የጽዱ ኢትዮጵያ የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ከንቲባ ጥራቱ በየነ፤ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚመጥኑና ከተማዋን ውብ፣ ጽዱና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ የሚያግዙ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል። በከተማዋ ከኮሪደር ልማት ሥራ ጋር በተያያዘ ሰፋፊ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች እንዲሁም በየአካባቢው የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች መገንባታቸውንም አመልክተዋል፡፡ ሃዋሳ ውበትና ጽዳት መለያዋ መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባ ጥራቱ፤ ከከተማዋ ዕድገትና ኢንቨስትመንት መስፋፋት ጋር ተያይዞ በቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት ላይ ውስንነቶች እንዳሉ ተናግረዋል። ይህንን ችግር ለመፍታት ከተማ አስተዳደሩ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፣ በ2019 ዓ.ም የከተማዋን አድገት የሚመጥን አዲስ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ሥፍራ ለመገንባት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ከከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር ተጣጥመው እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎችተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል። የሃዋሳ ከተማ የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ሹምባሻ በበኩላቸው በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ከአካባቢ ጥበቃ ሥራ ጋር የተሰናሰለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በከተማዋ በየመንደሩ ቆሻሻ የሚሰበስቡና ለይተው የሚያስወግዱ ማህበራትን በማደራጀት ጽዱ አካባቢን የመፍጠር ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከብክለት የጸዳ ከባቢና ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር አስተዋጽኦ እያደረገ ነው
Aug 28, 2026 234
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከብክለት የጸዳ ከባቢና ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን የግሎባል ፈንድ የአፍሪካ ተወካዮች ቢሮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ሄንሪ ፎሙንዳም ገለጹ። በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን 76ኛው የዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ኮሚቴ ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል። የአፍሪካ ሀገራት፣ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የጤና መሪዎች በተሳተፉበት መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ዲጂታልና ሰው ሠራሽ አስተውሎት የታገዘ የጤና ሥርዓት ግንባታ በሽታን በመከላከልና አክሞ በማዳን አቅም ለአፍሪካውያን ምሳሌ የሚሆን ጥረት እያደረገች መሆኑ ተመላክቷል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከ50 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ለግብርና ምርታማነት፣ ለመድኃኒት ቅመማና ለአየር ንብረት ደኅንነት ውጤት እያስመዘገበች መሆኑ ተገልጿል። በመድረኩ ላይ የተገኙት ዶክተር ሄንሪ ፎሙንዳም ለኢዜአ እንዳሉት፤ በአፍሪካ ጠንካራና ዘላቂ ዋስትና ያለው የጤና ሥርዓት ለመገንባት ትብብር ወሳኝ ነው። የአፍሪካውያን ዕውቀት፣ የተፈጥሮ ጸጋና በቂ የሰው ኃይል የጤና ፋይናንስና የአስተዳደር ሥርዓቱን በማዘመን የራሳቸውን ጠንካራ የጤና ተቋማት መፍጠር እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ የጤና እክሎችን በመቀነስ የዜጎችን በሕይወት የመኖር ምጣኔ እንደሚያሻሽል ተናግረዋል። በዚህም ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አፍሪካዊት ቀዳሚ ሀገር በመሆን ከብክለት የጸዳ ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገች መሆኑን ተናግረዋል። አፍሪካውያን የጤና ሥርዓታቸውን በራሳቸው አቅም ለመገንባት ከአጋር አካላት ጋር የሚኖራቸው ትብብር በትይዩ እንጂ ሰጪና ተቀባይ እንዲሆን መፍቀድ እንደማይገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። የአፍሪካን የጤና ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ከጤና የተሻገረ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ ራስን መቻል እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና በአህጉሪቷ የመድኃኒትና የሕክምና መገልገያ አምራች ኢንዱስትሪዎች መካከል ትስስር ለመፍጠር መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥርም አብራርተዋል።
ለትውልድ የሚተርፍ ውርስ፡የአረንጓዴ አሻራ ዘርፈ ብዙ አስተዋጽኦ
Aug 28, 2026 174
ድርቅ እና የደን መጨፍጨፍ ከኢትዮጵያ ጋር ለበርካታ ዓመታት ሲነሱ የቆዩ ጉዳዮች ናቸው። ኢትዮጵያ ይሄን ታሪኳን ለመቀየር ቆርጣ ከተነሳች ዓመታት ተቆጥረዋል።አረንጓዴ አሻራ-ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በአካባቢ ጥበቃ እና የማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ግንባር ቀደም የሆነ የለውጥ ሞተር ሆኗል። በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ብዝሃ ህይወትን ወደ ቀደመው ስፍራ ለመመለስ፣በረሃማነት ለመከላከል፣የደን ሽፋንን ከመጨመር አልፎ የአየር ንብረት ለውጥ የመከላከል ጥረቶች አስተዋጽኦ እስከ ማበርከት ደርሷል። የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች እና ከፓሪስ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ጋር በመሰናሰል ዘላቂ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ ኢኮኖሚ የመገንባት ትልም አለው። ኢኒሼቲቩ ድንበር ተሻጋሪ ተጽእኖ ያለው ነው ቢባል የተጋነነ አይሆንም።አረንጓዴ አሻራ በደን መልሶ ማልማት አማካኝነት ዛፎችን ወደ ይዞታቸው በመመለስ ወደ አየር ሊለቀቅ የሚችል በሚሊዮን ቶኖች የሚቆጠር ካርቦን ዳይ ኦክሳይድ አምቆ በመያዝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ካርቦንዳይ ኦክሳይድን ከከባቢ አየር የማስወገድ እና የማከማቸት ጥረት ውስጥ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የካርቦን ዳይኦክሳይድን አምቆ መያዝ እና ማከማቸት በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው። ድንበር ተሻጋሪው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአፍሪካ ቀንድ የመሬት መሸርሸርን ከመከላከል፣የደን ሽፋንን በመጨመር፣በረሃማነትን ከመከላከል እንዲሁም በአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የራሱን በጎ ሚና ተጫውቷል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ አየር ንብረት ለውጥ ውይይቶች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሯ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን በመቀነስ ረገድ እያበረከተ ያለው ሚና እውቅና የተሰጠው ነው። መልከ ብዙው አረንጓዴ አሻራ በአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ አዲስ አማራጭን ይዞ የመጣ እንደሆነም ይነገርለታል። ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አካባቢ ጥበቃ ስራ የውጭ እርዳታ ላይ ጥገኛ ከመሆን በሀገር ውስጥ አቅም ሀብት የማሰባሰብ ሞዴል መፍጠር ችሏል። ሀገር በቀል ፋይናንስ፣የማህበረሰብ ጉልበት እና የአይነት ድጋፎች ተዳምረው በአነስተኛ በጀት ፈጠራ የታከለበት የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ ማከናወን እንደሚቻል አሳይቷል። ኢትዮጵያ ከአረንጓዴ አየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (GCF)፣ የዓለም ባንክ፣የተባበሩት መንግስት የአየር ንብረት ለውጥ ፕሮግራም እና ሌሎች አጋሮች ለአካባቢ ጥበቃ ስራዎች የገንዘብ ድጋፍ እና የቴክኒክ ድጋፎችን አግኝታለች። የተገኘው ዓለም አቀፍ ድጋፍ የአካባቢ ጥበቃ ስራ በኢትዮጵያ የልማት ፖሊሲዎች የበለጠ እንዲተሳሰሩ አድርጓል። አረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥ ግቦችን ከኢኮኖሚ ልማት፣ ስራ ፈጠራ፣ አረንጓዴ ቱሪዝም እና ዘላቂ ግብርና ጋር በማስተሳሰር ሁሉን አቀፍ እይታን መፍጠር ጥሏል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሀገሪቷ የደን ሽፋን መጨምርም ጉልህ ሚና ተጫውቷል። መርሃ ግብሩ ከመጀመሩ በፊት የነበረው የሀገሪቱ የደን ሽፋን 17 ነጥብ 2 በመቶ ሲሆን ባለፈው አመት በተጠናው ጥናት ሽፋኑ 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። አረንጓዴ አሻራ ከ20 ዓመት በፊት ከአራት በመቶ በታች የነበረውን የኢትዮጵያን የደን ሽፋን መልሶ እንዲያንሰራራ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የተራቆቱ አካባቢዎችን በፍጥነት ተንከባክቦ ማዳንና ምርታማ በማድረግ፣ የተራቆተ መሬትን በእጽዋት የማልበስ ስራ ላይ ጉልህ አበርክቶ አለው። አረንጓዴ አሻራ የደን ሽፋንን ማሳደግ ብቻ ሳይሆን የደኖች ብዝሃ ህይወት ዳግም እንዲያብብና የማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ላይ የድርሻውን ተወጥቷል። በአረንጓዴ አሻራ ለደን እና ለውበት ከሚተከሉት ችግኞች ባሻገር በጥምር ደን እርሻ ለፍራፍሬ እና መኖ የሚውሉ ምግቦች በብዛት በማምረት የምግብ ዋስትና የማረጋገጥ ሂደት ውስጥ የበኩሉን ሚና እየተወጣ ይገኛል። ሲጠቃለል አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ከመትከል ዘመቻ ያለፈ ነው።የአየር ንብረት ለውጥን የመከላከል፣ዘላቂ ልማትን የማረጋገጥ እና ዓለም አቀፍ ትብብርን የመፍጠር ትልቅ ለውጥ ያለው ኢኒሼቲቭ ነው። በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት የአየር ንብረት ግቦች እንዲሳኩ በፖለቲካ ቁርጠኝነት፣በማህበረሰብ ተሳትፎ፣ በፈጠራ መፍትሄዎች እና ሁሉን አቀፍ ተግባራት አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚችሉም የሚያመላክት ተምሳሌታዊ ኢኒሼቲቭ እንደሆነም ሊሰመርበት ይገባል። ዓለም በአየር ንብረት ስጋቶች ውስጥ እየኳተነች ባለችበት ወቅት የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ልምድ የተስፋ ጮራ የሆነና አረንጓዴ ትራንስፎርሜሽን አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ስኬታማ ሊሆን እንደሚችል በተግባር አሳይቷል። ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ በተፈጥሮ ላይ እየሰራች ለትውልድ መጻኢ ጊዜን እየጠበቀች ነው።ይህ ተግባር ከሀገር አልፎ ድንበርን ተሻግሯል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 1430
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 1141
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 1418
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 2014
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
የስኬት መገለጫና የውጤት ማሳያዎች
Aug 28, 2026 181
አዲስ አበባ ነሀሴ 22/2018 (ኢዜአ) የስኬት መገለጫና የውጤት ማሳያዎች በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብና የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (Homegrown Economic Reform) እቅዶችን በመተግበር በበርካታ ዘርፎች መሠረታዊ ለውጦችን እና ስኬቶችን ማስመዝገብ ተችሏል። በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጂታል (አይሲቲ)፣ በማዕድን እና በቱሪዝም ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብታዊ አቅም ከማሳደግ ባሻገር የወደፊት ዘላቂ እድገት መሠረት ያኖሩ መሆኑን መናገር ይቻላል። በመሆኑም በአምስቱ ዋና ዋና ሴክተሮች የመጡ ውጤቶችና የተመዘገቡ ስኬቶችን በወፍ በረር እንቃኛለን። 1. በግብርና ዘርፍ የስንዴ ምርትና የውጭ ኤክስፖርት: የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መስፋፋት ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሰረት አስቀምጧል። ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የስንዴ ምርትን ወደ ውጭ ሀገር መላክ የቻለችበትን እመርታዊ ስኬትም አሳይቶናል። የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭን በመተግበር በወተት፣ በእንቁላል፣ በዶሮና የማር ምርት እንዲሁም በአትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ሩዝና ሻይ ልማትም ባለፉት አምስት አመታት እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል። አርሶ አደሩ የመሬትና የውሃ ሀብቶችን አቃፊ በሆነ መንገድ በመጠቀም በዓመት ሁለትና ሶስት ጊዜ ማምረት የሚችልበት አሰራር ተዘርግቷል። በዚህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ሁነኛ የገቢ ምንጭ የሆነበትን እድል ፈጥሯል። ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የመቻል አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል። በተለይም ደግሞ የቡና ምርታማነትና ጥራት በማደጉ ምክንያት በኤክስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማገኘት ተችሏል።   በዘርፉ በቀጣይም የግብርናውን ዘርፍ ይበልጥ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በሜካናይዜሽን በማስደገፍ ምርታማነትን የማሳደግ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። የመስኖ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት የዝናብ ጥገኝነትን ለመቀነስ መጣር እንዲሁም የግብርና ምርቶችን ጥራት በማሻሻልና በማቀነባበር ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ዋጋ ማሳደግ ተገቢ ይሆናል። 2. የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሀገራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ንቅናቄ በመፍጠር ቀደም ሲል ተቆልፈው የነበሩና በዝቅተኛ አቅምያመርቱ የነበሩ ፋብሪካዎች ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ ተደርጓል። የሀገር ውስጥ የምርት ፍላጎትን በመሸፈን ለውጭ ሀገር ምርቶች ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪም መቀነስ አስችሏል። ለሀገር ውስጥና ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ የህግና የአሰራር ሁኔታዎችን በመፍጠር በርካታ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ተችሏል። ከተገነቡት የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ፓርኮች (IAIPs) ጋር አርሶ አደሩን በማስሳሰር የግብአትና የምርት ትስስር እንዲጠናከር ተደርጓል። የአምራች ዘርፉ መስፋፋት ለብዙ ሺህ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች የሥራ እድል መፍጠር የታቸለበት ሆኗል። በቀጣይም የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በኃይል፣ በሎጂስቲክስና በግብአት አቅርቦት ሙሉ በሙሉ በመደገፍ ኤክስፖርትን ማሳደግ። የአምራች ኢንዱስትሪዎች 80% እና ከዚያ በላይ የሀገር ውስጥ ጥሬ ዕቃዎችን እንዲጠቀሙ ማበረታታት፣ በህዝብና በግል አጋርነት (PPP) አማካኝነት በትልልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ላይ የግሉን ዘርፍ አሳትፎ ማስፋፋት ትኩረት የሚደረግበት ይሆናል።   3. የዲጂታል (አይሲቲ) ዘርፍ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ስልት ስኬቶችን በማስቀጠል ወደ "ዲጂታል 2030" እቅድ መሸጋገር ተችሏል። በ"መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በሌሎች ፖርታሎች አማካኝነት ህዝባዊ አገልግሎቶችን በበይነ-መረብ (Online) የመስጠት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የዜጎችን መረጃ ማዕከላዊ የሚያደርግና ለፋይናንስ እንዲሁም ለሌሎች አገልግሎቶች መሠረት የሆነውን የፋይዳ መታወቂያ ፕሮጀክት በላቀ መልኩ ማሳካት ተችሏል። የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን የኮደር ስልጠናም የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ ታላቅ ሀገራዊ የስልጠና መርሃ ግብር ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።የዲጂታል አገልግሎቶች መዘርጋታቸው የፊት ለፊት ግንኙነትን በመቀነስ ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን በመከላከል የኢንቨስትመንት ምህዳሩን አሳልጧል። የቴሌኮም ዘርፍ ውድድር: የቴሌኮም ዘርፉን ክፍት ማድረግን ተከትሎ የኢንተርኔትና የኔትወርክ ተዳራሽነትንና ጥራትን በየገጠሩ የማስፋት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቶችን እና የባንክ አገልግሎቶችን ይበልጥ ዘመናዊና የተቀናጁ ማድረግም አስፈላጊ ይሆናል። የሀገሪቱን የዲጂታል መሠረተ ልማት ከሳይበር ጥቃቶች የመጠበቅ አቅምን ማጠናከር። 4. የማዕድን ዘርፍ በዘርፉ ይስተዋል የነበረውን ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ በመግታት ህጋዊ አሰራርና ቁጥጥር እንዲሰፍን ተደርጓል። የህግና መመሪያዎች ማሻሻያ በማድረግ የማዕድን ዘርፉን ለውጭና ሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ማራኪ የሚያደርጉ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ተደርገዋል። የወርቅ፣ የከሰል ድንጋይ፣ የሲሚንቶ ግብአቶችና የከበሩ ድንጋዮች ምርትን በማሳደግ ዘርፉ የሀገሪቱ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ እንዲሆን ተሰርቷል። በተለይም የከሰል ድንጋይ ምርትን በሀገር ውስጥ አምርቶ በመተካት ለፋብሪካዎች ግብአት ማቅረብ ተችሏል። 5. የቱሪዝም ዘርፍ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር)አነሳሽነት የተጀመሩት "ገበታ ለሸገር"፣ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች በመላ ሀገሪቱ በርካታ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን መገንባት ተችሏል። በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች የተከናወኑ የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበትና ለኑሮ ምቹነት ከመጨመራቸው ባሻገር ለከተማ ቱሪዝም ትልቅ እድል ፈጥረዋል። አዲስ አበባ በርካታ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችንና ኮንፈረንሶችን ባካሄደችበት የዲፕሎማሲና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷን አጠናክራለች።   የሀገሪቱን ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች የመጠበቅ፣ የማደስና ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራዎች በስፋት ተከናውነዋል። በድምሩ ባለፉት አምስት ዓመታት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጂታል፣ በማዕድን እና በቱሪዝም ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች ሀገሪቷን ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ምዕራፍ ማሸጋገር አስችለዋል። በመሆኑም እነዚህን ስኬቶች አጠናክሮ ለማስቀጠል የታቀዱትን የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች በተቀናጀ መልኩ መተግበር፣ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ እና የግሉን ዘርፍ አሳታፊነት ማሳደግ በቀጣይ አዲስ የሚመሰረተው መንግስት ዋነኛ የቤት ስራ ይሆናል።  
የአረንጓዴ አሻራ ስኬት፦ኢትዮጵያን የአየር ንብረት ጥበቃ ሞዴል ያደረገ ኢኒሼቲቭ
Aug 23, 2026 443
የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ የተጀመረው በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ነው። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እስከ አሁን ከ54 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እ.አ.አ በ2027 በኢትዮጵያ በሚካሄድበት ወቅት የተተከሉ ችግኞችን ብዛት 65 ቢሊዮን የማድረስ እቅድ ተይዞ እየተሠራ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች ያሉት ነው።ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የምግብ ምርታማነትን በማሳደግ፣ የደን ሽፋንን በመጨመር፣ የተራቆተ መሬትን ወደ ነባር ይዞታው እንዲመለስ በማድረግ እና አይበገሬ የአረንጓዴ ኢኮኖሚን በመገንባት ረገድ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። በዚህም በ2011 ዓ.ም 17.2 በመቶ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን፣ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በተከናወነው ሥራ ወደ 23.6 በመቶ ማደግ ችሏል።   ይህ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እውቅና አግኝቷል።በሁለተኛው የዓለም የምግብ ሥርዓት ጉባኤ እንዲሁም በአዲስ አበባ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ ሥራዋን ያስተዋወቀች ሲሆን፣ የአፍሪካ ሀገራትም ለአህጉሪቱ ትልቅ ተምሳሌት የሚሆን ኢኒሼቲቭ ሲሉ አድንቀውታል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታዘጋጅ መመረጧ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እያከናወነች ላለው ጥረት ዓለም አቀፍ እውቅና የተሰጠበት እና የሀገሪቱን የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ውጤት የሚያሳይ ነው። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በመለገስ የአካባቢ ጥበቃ የጋራ አጀንዳ መሆኑን በተግባር አሳይታለች።ይህም አረንጓዴ ዲፕሎማሲ በሀገራት መካከል በጎ ግንኙነትንና አዎንታዊ የቀጣናዊ ትስስር ድልድይን እየገነባ ይገኛል። የድንበር ተሻጋሪ የወንዝ ተፋሰሶችን በመንከባከብ፣ የታዳሽ ኃይል አቅርቦትን ለጎረቤት ሀገራት በማዳረስ እና በጋራ ድንበሮች አካባቢ የደን ሽፋንን በማሳደግ ረገድ እያከናወነችው ያለው ሥራ አህጉራዊ ሰላምና ትብብርን የሚያጎለብት አዲስ የዲፕሎማሲ መንገድ ከፍቷል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች የአህጉሪቱን ፍላጎትና ጥቅም ለማስከበር ግንባር ቀደም ተሟጋች ሆናለች።   ለአየር ንብረት ለውጥ አነስተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ነገር ግን ለጉዳቱ በከፍተኛ ሁኔታ የተጋለጡ የአፍሪካ ሀገራት ፍትሃዊ የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ እንዲያገኙ ድምፅ በመሆን አህጉራዊ መሪነቷን አስመስክራለች። ይህም አፍሪካውያን በራሳቸው ሀገር በቀል መፍትሔዎች የአየር ንብረት ጥበቃን ማረጋገጥ እንደሚችሉ ማረጋገጫ ሆኗል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና አምባሳደሮች የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ልማት እንቅስቃሴ ለአካባቢ ጥበቃ አርአያ የሚሆን ዓለም አቀፍ ሞዴል ሲሉ አድንቀውታል።   ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን ከመጠቀም፣የካርቦን ልቀትን ከመቀነስ እና ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መስፋፋት ጋር አጣጥማ የምታካሂደው እንቅስቃሴ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ እውቅና እንድታገኝ አስችሏታል።
ረብጣ ገንዘብ ከወጣባቸው ዝውውሮች እስከ አነጋጋሪ የህግ ለውጦች ፡ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲሱ የውድድር ዓመት ምን ይዞ መጣ?
Aug 21, 2026 437
በሙሴ መለሰ የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያን በጉጉት የሚጠብቀው የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ዛሬ በይፋ ይጀምራል። የዘንድሮው የውድድር ዘመን በሰኔ እና ሐምሌ ወራት የተካሄደውን የ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ተከትሎ፣ ለተጫዋቾች በቂ የእረፍት ጊዜ ለመስጠት ሲባል ከተለመደው አንድ ሳምንት ዘግይቶ እንዲጀምር ተደርጓል። የመክፈቻው ጨዋታ በኢምሬትስ ስታዲየም የባለፈው የውድድር ዘመን ሻምፒዮን አርሰናል እና ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ሊጉ በተመለሰው ኮቨንትሪ ሲቲ መካከል ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኤምሬትስ ስታዲየም ይካሄዳል። ይህ አዲስ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት በክረምቱ የተጫዋቾች ዝውውር መስኮት ላይ የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች ከፍተኛ ተሳትፎ አድርገዋል። እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት፣ የሊጉ ክለቦች ለተጫዋቾች ዝውውር ብቻ ከ2.14 ቢሊዮን ፓውንድ በላይ ወጪ አድርገዋል። ይህ የወጪ መጠን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከሌሎች የአውሮፓ አራት ታላላቅ ሊጎች (ስፔን፣ ጣልያን ጀርመንና ፈረንሳይ) በጥምረት ካወጡት የገንዘብ መጠን በላይ ሆኗል። ሞርጋን ሮጀርስ ከአስቶን ቪላ ወደ ቼልሲ በ117 ሚሊዮን ፓውንድ በመዘዋወር የክረምቱ ውዱ ተጫዋች መሆን ችሏል። ኤሊዮት አንደርሰን ከኖቲንግሃም ፎረስት ወደ ማንቸስተር ሲቲ በ116 ሚሊዮን ፓውንድ አምርቷል። በተጨማሪም ሳንድሮ ቶናሊ ከኒውካስል ወደ ቶተንሃም በ100 ሚሊዮን ፓውንድ፣ እንዲሁም ብሩኖ ጉማሬሽ ከኒውካስል ዩናይትድ ወደ አርሰናል በ75 ሚሊዮን ፓውንድ መዘዋወራቸው የክረምቱን የዝውውር ገበያ ከሚጠቀሱ ዝውውሮች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ከዝውውር ወጪው ባሻገር፣ የዘንድሮው የውድድር ዘመን በአዳዲስ አሰልጣኞች የታጀበ ሆኗል። በሊጉ ታሪክ ከፍተኛው በተባለ ደረጃ ዘጠኝ ክለቦች ውድድሩን በአዲስ አሰልጣኞች ይጀምራሉ። ፔፕ ጋርዲዮላ ማንቸስተር ሲቲን በገዛ ፈቃዱ መልቀቁን ተከትሎ የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አሁን ላይ በሊጉ ረጅም ጊዜ (ሰባት ዓመታት) የቆየው አሰልጣኝ ሆኗል። የቼልሲው ዣቢ አሎንሶ፣ የማንቸስተር ሲቲው ኤንዞ ማሬስካ እና የሊቨርፑሉ አንዶኒ ኢራኦላ ከአዳዲሶቹ አሰልጣኞች መካከል ይጠቀሳሉ። ማይክል ካሪክ በማንቸስተር ዩናይትድ እንዲሁም ሮቤርቶ ዴ ዜርቢ በቶተንሃም ሆትስፐርስ የመጀመሪያ ሙሉ የውድድር ዓመታቸውን ይጀምራሉ። የሊጉ የተሳታፊዎች ስብጥርን በተመለከተ፣ ኮቨንትሪ ሲቲ ከ25 ዓመታት በኋላ ከሃል ሲቲ እና ኢፕስዊች ታውን ጋር በመሆን ከታችኛው ሊግ አድገው ሊጉን ተቀላቅለዋል። በተቃራኒው ዌስትሃም ዩናይትድ፣ በርንሌይ እና ዎልቨርሃምፕተን ዋንደረርስ ባለፈው የውድድር ዘመን መውረዳቸው የሚታወስ ነው። በተጨማሪም የእንግሊዝ ክለቦች ባለፈው ዓመት በአውሮፓ ባሳዩት አስደናቂ ብቃት ምክንያት፣ በዚህ የውድድር ዘመን ክብረ ወሰን የሆነ ዘጠኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በአውሮፓ ውድድሮች ላይ ይሳተፋሉ። አርሰናል፣ አስቶንቪላ፣ ሊቨርፑል፣ ማንቸስተር ሲቲ እና ማንቸስተር ዩናይትድ በሻምፒዮንስ ሊግ የሚወዳደሩ ሲሆን፣ በርንማውዝ፣ ሰንደርላንድ እና ክሪስታል ፓላስ በዩሮፓ ሊግ እንዲሁም ብራይተን በኮንፈረንስ ሊግ አገራቸውን ይወክላሉ። የሊጉ አስተዳደር የክለቦችን የፋይናንስ ወጪ የሚቆጣጠር አዲስ የወጪ ገደብ (Squad Cost Ratio) መመሪያን ተግባራዊ አድርጓል። በዚህም መሠረት ክለቦች ለተጫዋቾች ደሞዝ እና ለዝውውር የሚያወጡት ጠቅላላ ወጪ ከገቢያቸው 85 በመቶ እንዳይበልጥ ተወስኗል። ህጉን የሚጥሱ ክለቦችም የነጥብ ቅነሳ ቅጣት ይገጥማቸዋል። የጨዋታ ፍጥነትን ለመጨመርና ሰዓት ማባከንን ለመግታት በርካታ አዳዲስ የዳኝነት ህጎች በይፋ ስራ ላይ ይውላሉ። በእጅ ውርወራ (Throw-in) እና በመልስ ምት (Goal-kick) ላይ ሰዓት ለሚያባክኑ ተጫዋቾች ዳኛው አምስት ሴኮንድ የሚቆጥር ሲሆን፣ ጊዜ ካለፈ እጅ ውርወራው ለተቃራኒ ቡድን ይሰጣል፤ የመልስ ምት ላይ ከሆነ ደግሞ የተቃራኒ ቡድን የማዕዘን ምት ያገኛል። ሌላው ሰዓት ማባከንን ለመቆጣጠር የወጣው ህግ ተጫዋቾች ታክመው ከወጡ በኋላ ወደ ሜዳ ለመመለስ ቢያንስ አንድ ደቂቃ ውጭ እንዲጠብቁ የሚያስገድደው ደንብ ነው። በተጨማሪም ተጫዋቾች በሚቀየሩበት ወቅት ከሜዳ ለመውጣት የ10 ሴከንድ ገደብ የተጣለባቸው ሲሆን፣ ይሁንና ጊዜው ካለፈ ተቀያሪው መግባት የሚችለው ጨዋታው በሚቀጥለው ጊዜ ሲቆም ብቻ ይሆናል። በዚህ የውድድር ዘመን የቪዲዮ ረዳት ዳኛ (VAR) ውሳኔዎችን ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ ትልቅ ማሻሻያ ተደርጓል። አንድ ተጫዋች በሁለተኛ ቢጫ ካርድ ከሜዳ ሲሰናበት አጠራጣሪ ከሆነ ቫር ጣልቃ የመግባት ስልጣን ተሰጥቶታል፤ እንዲሁም በጨዋታ ወቅት በቫር እና በሜዳ ላይ ዳኛው መካከል የሚደረጉ የድምፅ ውይይቶች በሊጉ የጨዋታ ማዕከል በኩል ለደጋፊዎች በቀጥታ ይፋ ይደረጋሉ። በአጠቃላይ፣ የዘንድሮው የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ከአዳዲስ የህግ ለውጦች፣ ከከፍተኛ የዝውውር ወጪዎች እና አዳዲስ የአሰልጣኞች ሹመት ጋር ተያይዞ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረትን ስቧል። አርሰናል የዋንጫ ክብሩን ለማስጠበቅ፣ ማንቸስተር ሲቲ ያለ ፔፕ ጋርዲዮላ አዲስ ምዕራፍ ለመጀመር፣ እንዲሁም አዳዲስ አሰልጣኞችና ክለቦች ህልማቸውን ለማሳካት የሚያደርጉት ፍልሚያ የእግር ኳስ አፍቃሪያን እስከ ግንቦት ወር መጨረሻ ድረስ የሚዘልቅ አስደሳች እና አጓጊ የእግር ኳስ ጊዜን እንደሚያሳልፉ አያጠራጥርም።
ቡሄ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ምስረታ ታሪካዊ ቁርኝት
Aug 19, 2026 639
በሙሴ መለሰ ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን የቡሄ በዓል በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ባለበት በዚህ ዕለት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አጀማመሩንና ምስረታውን ከዚህ በዓል ጋር ያለውን የጠበቀ ትስስር ወደ ኋላ መለስ ብሎ የሚታወስበት ነው። የክለቡ ምስረታና የቡሄ በዓል (የሆያ ሆዬ ጨዋታ) ቀጥተኛና የማይነጠል ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፣ ክለቡ በመስረታው ወቅት የነበረበትን የፋይናንስ እጥረት ቀርፎ የመጀመሪያውን ማሊያ ለመግዛት የበቃው በዚህ ዕለት በተሰበሰበ የሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ነበር። የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን መጀመሪያ ሲጠነሰስ በጆርጅ ዱካስና በአየለ አትናሽ አማካኝነት የነበረ ቢሆንም፣ ክለቡን በይፋ አደራጅቶ ለማቋቋም ግን የግድ የፋይናንስ አቅም ወይም ገንዘብ ያስፈልግ ነበር። ሆኖም ግን በሃገር ፍቅር ስሜት የተነሱት ዘጠኙ ወጣቶች ማለትም አየለ አትናሽ፣ ጆርጅ ዱካስ፣ ዮሐንስ ጥላሁን፣ ገብረመድህን ተፈሪ፣ ተፈራ ገብረእግዚአብሔር፣ ዓለማየሁ እጅጉ፣ መኮንን ደምሴ፣ አስፋው ያዕቆብ እና ክልቱ አያኖ ክለቡን በሚመሰርቱበት ወቅት ቤሳ ቤስቲን እንኳ ኪሳቸው ውስጥ ስላልነበራቸው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ተሰብስበው በሰፊው ተወያዩ። በዚህ የውይይት ወቅት ነው ገንዘብ ለማግኘትና የክለቡን መመስረት እውን ለማድረግ የቡሄ ቀን እጅግ መልካምና ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን የተረዱት። ዘጠኙ ወጣቶች በአንድ ድምፅ ተስማምተው በታሪካዊው የቡሄ ዕለት ማለትም ነሐሴ 13 ቀን 1927 ዓ.ም. በጋራ በመሆን ቡሄ ጨፍረው (ሆያ ሆዬ ብለው) በሚያገኙት ማናቸውም ነገር የክለቡን የመጀመሪያ ማሊያ ለመግዛት ቁርጥ የሆነ ውሳኔ ላይ ደረሱ። በዚያን ጊዜ የነበረው የባህል ልማድ አሁን ካለው የተለየ በመሆኑ፣ ቡሄ ሲጨፈር የሚሰጠው ጥሬ ገንዘብ ሳይሆን ሙልሙል ዳቦ ነበር። በመሆኑም ዘጠኙ ተጫዋቾችና መስራቾች ቀደም ሲል ከሚጨፍሩበትና ለምደውት ከነበረው አካባቢ ራቅ ብለው በመንቀሳቀስ በየቤቱ በር እያንኳኩ በደመቀ ሁኔታ ጨፈሩ፤ በዚህም ጥረታቸው በርካታ ቁጥር ያለው የሙልሙል ዳቦ በአንድነት ማሰባሰብ ቻሉ ታሪካዊውን ስራ ሰሩ። ይሁን እንጂ የተሰበሰበውን ይህንን በርካታ ዳቦ ወደ ጥሬ ገንዘብ ለመቀየር አዲስ አበባ ውስጥ ወደሚገኘው ሰራተኛ ሰፈር ለሚገኙ ወዛደሮች ለመሸጥ ዳቦውን በከረጢት ይዘው ጉዟቸውን ጀመሩ። በዚህ የጉዞ መስመር ላይ ሳሉ ግን ያልተጠበቀ ፈተና ገጠማቸው፤ በመንገድ ላይ ያገኟቸው “ዱርዬዎች” ከተሰበሰበው ዳቦ ላይ የተወሰነውን ነጠቋቸው። ወጣቶቹ ተስፋ ሳይቆርጡ ጉዟቸውን በመቀጠል የተረፈውን ዳቦ ለሰራተኛ ሰፈሩ ወዛደሮች በመሸጥ ማሊያ መግዣ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ በእጃቸው አስገቡ። ከዳቦው ሽያጭ የተገኘችው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን በወቅቱ መገበያያ በትክክል ሁለት ጠገራ ብር ነበረች። የክለባችው የመጀመሪያ መለያ ቡናና ነጭ ነበር። ቡናና ነጭ መሊያን የገዙት ግን ፈልገው አልነበረም በቂ ገንዘብ ስላልነበራቸው በሁለት ጠገራ ብር ከፒያሳ «ግሪካዊ አውግስታስ ዱስ» ከተባለ ሱቅ በርካሽ ስላገኙት ነበር። ይህ በቡሄ ዕለት የተጀመረው ታሪካዊ የማሊያ ግዢ በኋላ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በታህሣሥ ወር 1928 ዓ.ም. በይፋ ተመሠረተ። ክለቡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለብ በመሆን ታሪካዊ ማዕረግንና ቀዳሚነትን ተቀዳጀ። በ1928 ዓ.ም. በይፋ የተመሰረተው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በታሪኩ የመጀመሪያውን የሜዳ ጨዋታ ያደረገው ከ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ነበር። በዚሁ ታሪካዊ የመጀመሪያ ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። በዕለቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠንካራ ተፎካካሪ ከነበረው የ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ለመጫወት ወደ ሜዳ ሲያመራ፣ አስቀድመው ከተመረጡትና ቡድኑን ካደራጁት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ባልታወቀ ምክንያት ሳይመጣ ቀረ። በዚህ ድንገተኛ መቅረት ምክንያት ቡድኑ በሰው ጎደሎ ለመጫወት በተገደደበት ወሳኝ ሰዓት፣ መስራቾቹ በሜዳው አቅራቢያ መንገድ ላይ ሲጫወት ያገኙትን አንድ ታዳጊ ወጣት ተመለከቱ። ይህ ታዳጊ በወቅቱ ገና የ14 ዓመት ዕድሜ የነበረውና በኋላ ላይ የኢትዮጵያ ስፖርት ባልደረባ የሆነው ይድነቃቸው ተሰማ ነበር። ወጣቶቹም ያለ ምንም ቅድመ ዝግጅት ቡድኑን እንዲሞላ ድንገት ጋበዙት፤ እርሱም የቀረበለትን ጥሪ በደስታ ተቀብሎ በአጋጣሚ ወደ ሜዳ ገባ። ያለ ምንም ልምምድና ዝግጅት በድንገት የተሰለፈው ይድነቃቸው ተሰማ፣ በሜዳ ላይ ያሳየው አስደናቂ ችሎታና ቅልጥፍና ሁሉንም ያስገረመ ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ታሪካዊ ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ፣ ለክለቡ የመጀመሪያውን ድል ያስገኙትን ሁለቱንም ታሪካዊ የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ይኸው መንገድ ላይ ተገኝቶ በድንገት የተሰለፈው ታዳጊ ይድነቃቸው ነበር። ይህ ብቃት ገና በታዳጊነቱ በክለቡ ውስጥ ያለውን የማይተካ ቦታ ከማረጋገጡም በላይ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን የድል ጉዞ በደመቀ ሁኔታ እንዲጀመር አድርጓል። ቡሄ በዓል እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ያላቸው ታሪካዊ ቁርኝት የክለቡን ጥልቅ ህዝባዊና ባህላዊ መሰረት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቀዳሚ ፋና ወጊ የሆነው ይህ ታላቅ ክለብ፣ በታሪካዊቷ የነሐሴ 13 ቀን የቡሄ ዕለት የመስራቾቹ የ"ሆያ ሆዬ" ጨዋታና ከተሰበሰበው ሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ባገኟት ሁለት ጠገራ ብር የመጀመሪያውን ቡኒና ነጭ ማሊያ መግዛቱ፣ ክለቡ ከህዝብ ማህፀን የወጣ የህዝብ ሀብት መሆኑን ያረጋግጣል። ይህ ከባህልና ከትውፊት ጋር የተቆራኘ አስደናቂ አጀማመር፣ ከጊዜ በኋላ በ1928 ዓ.ም. ለይፋዊ ምስረታው በር ከፋች ከመሆኑም በላይ፣ በታሪካዊው የመጀመሪያ ጨዋታ ላይ እንደ ይድነቃቸው ተሰማ ያሉ የአፍሪካ እግር ኳስ ታላላቅ መሪዎችና ድንቅ ተሰጥኦዎች እንዲፈጠሩ መሰረት የጣለ የኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ነው።
ትንታኔዎች
የቀይ ባህር ደህንነት እና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ሚና
Aug 29, 2026 668
(በሙሴ መለሰ) በቀይ ባሕርና በኤደን ባሕረ-ሰላጤ ቀጣናዊ ሰላምና ፀጥታን ለማረጋገጥ በሚደረገው ዓለም አቀፍ ጥረት ውስጥ ኢትዮጵያ የሚኖራት ሚና ከፍተኛ ነው። የኢትዮጵያ አብዛኛው ወጪና ገቢ ሸቀጦች በባህር በር በኩል የሚተላለፉ በመሆኑ፣ በቀይ ባህር እና በኤደን ባህረ ሰላጤ የሚከሰቱ የፀጥታ መደፍረሶች ወይም የሎጂስቲክስ መስተጓጎሎች በቀጥታ በሀገሪቱ ብሔራዊ ኢኮኖሚ ላይ የራሱን ተጽዕኖ ማሳረፉ የማይቀር ነው። በሆርሙዝ ሰርጥ የተከሰተውን የጸጥታ ቸግር ተከትሎ የተለያዩ የዓለም ሃገራት የቀይባህር መስመር ከባቤል ሜንደብ እስከ ስዊዝ ቦይ ድረስ ያለው ደህንነት አሳስቧቸዋል። ይሄንን ስጋት ለማቃለልም ሆነ የተለያዩ ፍላጎቶቻቸውን መነሻ በማድረግ አንዳንድ ሃገራት በቀጣናው ካሉ የባህር ተጋሪ መንግስታት ጋር በመሆን የመሰረቷቸውን የጦር ሰፈሮች ቢያጠናክሩም አሁንም ቀጣናው በባህር ላይ ውንብድና፣ በህገ-ወጥ ንግድና የሰዎች ዝውውር ወንጀል ለስጋት የተጋለጠ ሆኖ ይገኛል። የአፍሪካ ቀንድ ሰላም ከቀይ ባህር ደህንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ መሆኑን በጽኑ የምታምነው ኢትዮጵያ፣ ድንበር ተሻጋሪ የፀጥታ ስጋቶችን ለመከላከል በሚደረጉ የባለብዙ ወገን ውይይቶች ላይ በመሳተፍ የበኩሏን አስተዋጽኦ ታበረክታለች። በተለይም ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን፣ የጦር መሳሪያ እና የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውርን እንዲሁም የባህር ላይ ወንጀሎችን በጋራ ለመመከት የቀጣናው ሀገራት የተቀናጀ ምላሽ እንዲኖራቸው ድጋፍ ታደርጋለች። ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድ አገራት ጋር ያላት መልክዐ ምድራዊ ትስስር እና የፀጥታ አጋርነት በቀይ ባህር ቀጣና መረጋጋት ውስጥ ወሳኝ ድርሻ አለው። በቀጣናው የሚከሰቱ ፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች እና የጸጥታ ችግሮች በቀጥታ በሀገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ በመሆናቸው፣ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ሰላምን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የትብብር አማራጭን ተከትላ እየሰራች ትገኛለች። የአፍሪካ ቀንድና የቀይባሕር ደኅንነት ሊለያዩ የማይችሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። ኢትዮጵያ በሕዝብ ብዛቷ፣ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴዋና በጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጧ በቀጣናው ትልቅ ድርሻ ያላት በመሆኑ፣ በሚደረጉ የማሪታይምና የደኅንነት ውይይቶች ላይ የምታደርገው ንቁ ተሳትፎ ለቀጣናው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ አስፈላጊ ነው። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን ሰፊ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚዊ ተጽዕኖ በመጠቀም፣ ስትራቴጂያዊ የንግድ መስመሮችን ከስጋት ነፃ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑ በቅርቡ በናይሮቢ በተካሄደው ዓለም አቀፍ መድረክ በግልጽ ታይቷል። በኬንያ ናይሮቢ በተካሄደው አምስተኛው የቀይ ባህርና የኤደን ባህረ ሰላጤ የባህር ላይ ህግ ማስከበር ውይይት (Maritime Law Enforcement Dialogue) ላይ፣ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅሞችን የሚያስጠብቅ ተሳትፎ አድርጓል። ይህም ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና የኢኮኖሚ ትስስር ላይ ያላትን ሚና እና ባለቤትነት አሳይቷል። ለኢትዮጵያ የባህር በር ደህንነት የህልውና ጉዳይ ነው። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ተወካይ ካፒቴን ክብሩ መስፍን እንደገለጹት፣ የባሕር ላይ ሰላም መደፍረስ በቀጥታ የአገሪቱን ብሔራዊ ኢኮኖሚ ይነካል። አብዛኛው የሀገሪቱ ወጪና ገቢ ንግድ በባህር ላይ የሚካሄድ በመሆኑ፣ በቀይ ባህር ላይ የሚከሰቱ የባሕር ላይ ውንብድናዎችና ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች የንግድ ፍሰቱን እንዳያስተጓጉሉ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። ካፒቴን ክብሩ አክለውም፣ የመርከቦች መድን ዋስትና መናርና የሸቀጦች መዘግየት የሀገሪቱን የንግድ ተወዳዳሪነት እንዳይፈታተኑ፣ ጠንካራና የተቀናጀ የባህር ላይ ቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። ይህን ዓለም አቀፋዊ ስጋትን ለመመከት ኢትዮጵያ የጋራ መፍትሔዎችን በማቅረብ ረገድ ግንባር ቀደም ናት። በተለይም ከጎረቤት አገራት ጋር በመቀናጀት "ብሔራዊ የማሪታይም መረጃ ማዕከል" (National Maritime Information Centre) ለመመስረት ያቀደችው ስትራቴጂ፣ ሀገሪቱ ለቀጣናው መረጋጋት ያላትን የረጅም ጊዜ ራዕይ የሚያሳይ ነው። መረጃን በጋራ መለዋወጥና የተቀናጀ የሕግ ማስከበር እርምጃ መውሰድ ለዚህ ስኬት ዋነኛው መሳሪያ እንደሆነ ኢትዮጵያ በጽኑ ታምናለች። በቀይ ባህርና በኤደን ባህረ-ሰላጤ የሚስተዋሉ እንደ ሕገ-ወጥ የሰዎችና የዕፅ ዝውውር እንዲሁም ሕገ-ወጥ አሳ ማጥመድ ያሉ ስጋቶች ድንበር ተሻጋሪ በመሆናቸው፣ እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ቀጣናዊ ኃይሎች ተሳትፎ የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡን ትኩረት ስቧል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአደንዛዥ ዕፅና ወንጀል ጉዳዮች ቢሮ (UNODC) የቀጣናው አስተባባሪ ሞስታፋ ኤልባና እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላት የፖለቲካና የኢኮኖሚ አቅም ዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አስተማማኝና የተረጋጉ እንዲሆኑ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው። በቀይ ባህር ቀጣና ያላትን ስትራቴጂካዊ ጥቅም ለማስጠበቅና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ዲፕሎማሲያዊና ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአደንዛዥ ዕፅና ወንጀል ጉዳዮች ቢሮ (UNODC)፣ ኢንተርፖል እና ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት (IOM) የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዲሁም ከጎረቤት ሀገራት ጋር በቅርበት በመሥራት ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና ጸጥታ ላይ ያላትን የመሪነት ሚና በታሪካዊ ኃላፊነትና በሕግ አግባብ እያስጠበቀች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የባህር ኃሃይልን ጨምሮ በጥብቅ ዲሲፕሊኑ እና በመፈጸም አቅሙ የሚታወቅ ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት ገንብታለች። ይሄ ሰራዊት በተለያየ ጊዜ ችግር ላጋጠማቸው ሃገራት ባሳየው የሰላም ማስከበር ሚናው በውጤታማነቱ የተመሰከረለትም ነው። የቀጣናውን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ ሃይል አስፈላጊ ስለሆነም በቅርብም በሩቅም ያሉ ሃገራት የኢትዮጵያን የባህር ላይ ህልውና በበጎ ይመለከቱታል። ለዚህም በቅርቡ በአንድ የሃገር ውስጥ ሚዲያ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ የባብኤል ሜንደብን እና የቀጣናውን ሰላም ለማስጠበቅ ሃገራቸው በቂ አቅም ስለሌላት የሌሎች እገዛ አስፈላጊ መሆኑን የተናገሩት የጅቡቲ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ፋይናስ ሚኒስትር ኢሊያስ ሙሳ ዳዋሌህ ገለጻ አንዱ ማሳያ ነው። እነዚህ ሁሉ ጉዳዮች አመላካች የሚሆኑት ያለ አግባብ ከባህሩ የተገፋችውና መብቷን የምትጠይቀው ኢትዮጵያ ያላት ዘርፈ ብዙ ዓቅም ለቀጣናውም ለራሷም ሰላምና ደህንነት መረጋገጥ ወሳኝ ሚና ያላት መሆኑን ነው።
የኢትዮጵያ አዲሱ የቱሪዝም ከፍታ!
Aug 29, 2026 173
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ከሀገሪቷ ልዩ ፀጋዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ሀገሪቱ ያሏት ጉምቱ ታሪክ፣ ብዝሃ ባህል እና ልዩ የቱሪዝም መዳረሻዎች ለአፍሪካ ስልጣኔ ያላትን ታላቅ ድርሻ የሚያመላክቱ ናቸው። ከላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንስቶ እስከ አክሱም ሀውልትና የጁገል ግንብ ድረስ ያሉት ቅርሶች የኢትዮጵያን የታሪክ ጥልቀት እና የባህል ትሩፋቶች በግልጽ ያሳያሉ። እነዚህ ታሪካዊ ሀብቶች በአሁኑ ወቅትም የውጭ ጎብኚዎች፣ ተመራማሪዎች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ቀልብ መሳባቸውን ቀጥለዋል። ከታሪክ ሀብቶቿ ባለፈም ማራኪው የመልክዓ ምድር አቀማመጥ፣ ብቅ ያሉ የዱር እንስሳቶች እና የዜጎች እንግዳ ተቀባይነት የአኗኗር ዘይቤ ለዘርፉ ዕድገት ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። መንግስት ቱሪዝምን እንደ አንድ ዋነኛ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመውሰድ ስትራቴጂካዊ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተቀረጹት የ"ገበታ ለሸገር"፣ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን እምቅ የቱሪዝም ሀብት ከማውጣት ባለፈ የገቢ መጠንን በማሳደግ ረገድ ጉልህ ለውጥ እያስመዘገቡ ነው። ከዚህም መካከል በሶማሌ ክልል በደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ በዋቢ ሸበሌ ወንዝ ዳርቻ ተገንብቶ በቅርቡ የተመረቀው እና የ"ገበታ ለትውልድ" አካል የሆነው የሸበሌ ሪዞርት አንዱ ማሳያ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምርቃቱ ወቅት እንደገለጹት፣ ሪዞርቱ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የገባነውን ቃል በተግባር ያረጋገጠ የምስራቁ የሀገራችን ክፍል ትልቅ ማሳያ ሥራ ነው። ይህ ስራ በታችኛው የዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ አካባቢ ለአካባቢው ማህበረሰብ የስራ እድል የፈጠረና የክልሉን የቱሪዝም ገጽታ የቀየረ ነው። በተጨማሪም በመዲናዋ አዲስ አበባ የተገነቡት የወዳጅነት አደባባይ፣ አንድነት ፓርክ፣ ሳይንስ ሙዚየም እና አብርሆት ቤተ-መጻሕፍት አዳዲስና ተመራጭ የከተማ ቱሪዝም (Urban Tourism) መዳረሻዎች ሆነዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በዋና ከተማዋ የተከናወነው ሰፊው የኮሪደር ልማት ሥራ የአዲስ አበባን መልክ በአዲስ ሁኔታ በመግለጥ፣ ከተማዋን ለሰው ልጅ ምቹ፣ ውብ እና የጎብኚዎች ዓይን ይበልጥ የሚያርፍባት የቱሪስት ማዕከል አድርጓታል። ከታሪካዊ ቅርሶች ጥበቃ አንጻርም እድሳት የተደረገላቸው ብሔራዊ ቤተ መንግስት (ኢዮቤልዩ)፣ የጎንደር የአፄ ፋሲል አብያተ መንግስታት፣ የጅማ አባጅፋር ቤተመንግስት እና የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ለዘርፉ መነቃቃት የጎላ አበርክቶ እያበረከቱ ይገኛሉ። ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ በቅርቡ በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገቡት የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር እና የባልካሌ ውብ ተፈጥሮአዊ ጥንታዊ ቅርሶች የኢትዮጵያን የቱሪዝም ካርታ ይበልጥ አበልጽገውታል። ይህ ዓለም አቀፋዊ እውቅና የሀገሪቱን የባህል እና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጥረት ማሳደጉ ብቻ ሳይሆን፣ ወደ እነዚህ አካባቢዎች የሚመጡ የውጭ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎችን ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ የቱሪዝም ገቢን ለማሳደግ አስችሏል። በሌላ በኩል፣ የቱሪዝም ዘርፉን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ የአቪዬሽን እና የእንግዳ ተቀባይነት (Hospitality) አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ መሆናቸው ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ መዳረሻ ማብዛት፣ የኤሌክትሮኒክስ ቪዛ (e-Visa) አሰጣጥ መዘመኑ እና ወደ ተለያዩ የመዳረሻ አካባቢዎች የሚደረጉ የትራንስፖርት አማራጮች መቃናታቸው ጎብኚዎች ያለ ምንም እንግልት ሀገሪቱን እንዲጎበኙ መንገድ ከፍቷል። ይህም ሀገሪቱ በኮንፈረንስ ቱሪዝም ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ ስብሰባዎች ተፈላጊ ማዕከል እንድትሆን አስችሏታል። በተጨማሪም የዲጂታል ቱሪዝም ፕሮሞሽን እና የቅርሶች ጥበቃ ስራዎች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደገፋቸው ለዘርፉ አዲስ ምዕራፍ አጎናጽፎታል። በማህበራዊ ሚዲያ እና በዲጂታል አማራጮች የሚሰሩ ማስተዋወቂያዎች የኢትዮጵያን ገጽታ ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በአዲስ መልክ አስተዋውቀዋል። እነዚህ የተቀናጁ የልማት፣ የጥበቃ እና የማስተዋወቅ ስራዎች ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን በመላው አህጉር ቀዳሚ የቱሪዝም መዳረሻ የመሆን ራዕይዋን በተግባር እያረጋገጡት ይገኛሉ። ይህንን የመንግስት ጥረት ተከትሎም ከባለሀብቶች እንዲሁም ከዓለም አቀፍ የዘርፉ ተዋንያን የሚመጣው ተሳትፎና የኢንቨስትመንት ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መጥቷል። በአጠቃላይ እነዚህ ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች፣ የታሪካዊ ቅርሶች ጥገና እና የተፈጥሮ መስህቦች ጥምረት የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ለኢኮኖሚ እድገት እና ለዘላቂ ልማት ያለውን ድርሻ ወደ ላቀ ደረጃ እያሳደጉት ይገኛል።
የኢትዮጵያውያን የወል እውነት- ሀገራዊ ምክክር
Aug 28, 2026 520
በሙሴ መለስ ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የጋራ መኖሪያ እና የብዝሃነት ውበት ደምቆ የሚታይባት ሀገር ናት ። ዛሬ ላይ ለመድረስም በርካታ ውጣ ውረዶችን፣ እና የታሪክ ምዕራፎችን ተሻግራለች። በነዚህ ምዕራፎች ውስጥም በአብሮነትና በጋራ ሃገራዊ እሳቤ ከተገነቡት የጋራ ማንነቶች ባልተናነሰ መልኩ ያጋጠሙ የታሪክ ስብራቶች የልዩነት እና ያለመግባባት መንስኤ የሚሆኑበትን አጋጣሚም አስተናግዳለች። ልዩነቶችን በጉልበት ወይም በኃይል ሳይሆን፣ በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር እና ከነጣይ ትርክት ይልቅ ወደ ሃገራዊ መግባባትና የጋራ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ብሔራዊ መግባባትን ለማምጣትም ሃገራዊ ምክክሩ የራሱን ቁልፍ ሚና በመወጣት በሃገራችን ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑ ይታወቃል። ከአራት ዓመታት በፊት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ሀገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ህዝባዊ ውይይቶችን በማድረግ የህብረተሰቡን አጀንዳዎች በባለቤትነት የማሰባሰብ ሂደቱን በስኬት አከናውኗል። የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ማህበራት፣ ምሁራን፣ ዳያስፖራዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ መድረክ የተሳተፉበት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ለ46 ቀናት ተካሄዶ በስኬት መጠናቀቁ ተበስሯል። ይህ ጉባኤ ዜጎች ሃሳባቸውን በነፃነት የገለጹበት፣ የጋራ መግባባት ላይ የደረሱበት በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥም የጠመንጃ የበላይነትን በማስቀረት፣ የሀሳብ የበላይነትና የሰላማዊ የውይይት ባህልን ለማስፈን ምቹ ምህዳር የፈጠረ አካታች አካሄድ ነው። ከጉባኤው የተገኙ ምክረ-ሐሳቦችና የተገኙት ልምዶች ወደ ተግባር እየተሸጋገሩ፣ በየደረጃው በሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል ውይይቱ ተጠናክሮ የሚቀጥልበትን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍትም ነው። የጋራ ትርክት ህዝቦች በታሪካቸው፣ በአሁኑ ሁኔታቸው እና በወደፊት ዕጣ ፈንታቸው ላይ ያላቸው የጋራ መረዳትና ስምምነት ሲሆን ይህም አብሮነትን ለማጎልበት ጠንካራ መሰረት ይጥላል። ለዘመናት በጦርነት፣ በኃይልና በፖለቲካ ሽኩቻ ሲንከባለሉ የቆዩ የትርክት ስብራቶችም ከጠመንጃ ይልቅ በሰላማዊ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ክርክር ለመፍታት ስለመቻሉም ትልቅ ማሳያ ነው። በምክክሩ ላይ በመላው ሃገሪቱ አሉን የሚሏቸውን ጥያቄዎችና ቅሬታዎች በኃይል በጦር መሳሪያ ለመፍታት ነፍጥ አንግበው ሲታገሉ የነበሩ አካላት ሁሉ እንዲሳተፉ መደረጉም የሒደቱን ስኬታማነት ለዓለም ማህበረሰብ ያሳየ ነው። ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች፣የፖለቲካ አመለካከቶችና የኅብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ አራት ሺህ ተመካካሪዎች የየራሳቸውን የተናጠል ፍላጎት ብቻ ከማንጸባረቅ ተቆጥበው በተለዩ ስምንቱ አበይት አጀንዳዎች ላይ በጋራ መስማማታቸውም የወል ትርክት ግንባታን የውጤታማነት ጉዞ ስኬት በተግባር የገለጠ ነው። ይህ ለግል ወይም ለቡድን ጥቅም ሳይሆን ለሀገር ህልውና እና ለጋራ ዕድገት ቅድሚያ የመስጠት ትልቅ የፖለቲካ ብስለትም ነው። ይህ ሂደት እያንዳንዱ ዜጋ በሀገሩ ላይ ሙሉ ባለቤትነትና ደህንነት እንዲሰማው የሚያደርግ ሲሆን የጋራ አገርና የጋራ ዕድል አለን የሚለውን እሳቤ በማጉላትም የወል ትርክትን በጽኑ መሠረት ላይ ይገነባል። ምክክሩ በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን (Elites) መካከል ብቻ የተደረገ ውይይት ሳይሆን እስከ ወረዳ ድረስ ያሉትን የታችኛውን የህብረተሰብ ክፍሎች፣ አርሶ አደሮችን፣ አርብቶ አደሮችንና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ መሆኑም ትልቅ ትርጉም አለው። ከሕዝብ ቀጥተኛ ተሳትፎ የፈለቁት ምክረ ሀሳቦች ለሀገራዊ ትርክት መጠንከር ወሳኝ ሚና ከመጫወት ባለፈ ሂደቱ በህዝቡ ዘንድ ሙሉ ተቀባይነት ያለው እንዲሆን ያደርገዋል። ምክክሩ ያረጋገጠው ትልቁ እውነት የኢትዮጵያውያን ዕጣ ፈንታ የተሳሰረ መሆኑንና የወል ትርክት ግንባታ የሀገር ህልውና ዋስትናነቱን ነው። ልዩነቶችን ውበት፣ ውይይትን ደግሞ መሳሪያ በማድረግ የተጀመረው ይህ ጉዞ ኢትዮጵያ በቀደመ ታሪኳ የገጠሟትን የታሪክ ስብራቶች በመጠገን ወደ ዘላቂ ብልጽግና፣ ዲሞክራሲና እውነተኛ አንድነት እንድትሸጋገር ያስችላታል።
የኢትዮጵያ የከፍታ ጉዞ ማሳያ የአፍሪካውያን ኩራት - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
Aug 27, 2026 310
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከንግድ ተቋምነት ባለፈ የአፍሪካውያንን አንድነት፣ የነፃነት ታሪክና የጋራ ብልጽግና ስትራቴጂን በሰማይ ላይ የገነባ እውነተኛ የፓን አፍሪካዊነት ተምሳሌት ነው። አህጉሪቱ ገና ከቅኝ አገዛዝ ቀንበር ባልተላቀቀችበትና የእርስ በእርስ ትስስር በሌለበት እ.አ.አ ከ1945 ጀምሮ የአፍሪካን ሕዝቦችና መሪዎች በማገናኘት የታሪክ ህያው ምስክር ሆኖ አገልግሏል።ይህ አየር መንገድ፣ የአፍሪካ አዲስ መንፈስ የሚለውን መፈክሩን በተግባር ያረጋገጠ ብሔራዊና አህጉራዊ ኩራትም ነው። አየር መንገዱ ለአፍሪካዊያን የጋራ ዕድገት የሚሠራ መሆኑን የሚያረጋግጠው ዋነኛው ተግባሩ፣ የገንዘብና የቴክኒክ አቅም አንሷቸው የፈረሱ ወይም የተቸገሩ የሌሎች አፍሪካ ሀገራትን ብሔራዊ አየር መንገዶች በጋራ ባለቤትነት መልሶ የማቋቋምና የማጠናከር ዘላቂ ስትራቴጂው ነው። በዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ትርፋማና ግዙፍ ተቋም ከመሆን ባለፈ የአህጉሪቱን የአቪዬሽን ዘርፍ በጋራ ለማሳደግ የአፍሪካ አየር መንገዶችን የማቋቋምና የመደገፍ” ስትራቴጂካዊ ሥራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል። ተቋሙ ከአፍሪካ አየር መንገዶች ማህበር (AFRAA) እና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መንግስታት ጋር በመተባበር በአህጉሪቱ ዘርፈ ብዙ ስኬቶችን አስመዝግቧል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የባለቤትነት ድርሻ በመያዝ እና የማኔጅመንት (የአመራር) አገልግሎት በመስጠት በርካታ አየር መንገዶችን በማቋቋምና በማጠናከር ቀዳሚውን ሚና እየተጫወተም ይገኛል። በዚህም በምዕራብ አፍሪካ ቶጎ ላይ መቀመጫውን ያደረገው አስካይ (ASKY) አየር መንገድ፣ የማላዊ አየር መንገድ፣ የዛምቢያ አየር መንገድ እና የኮንጎ አየር መንገድ የጊኒ አየር መንገድ እና ሌሎችም የአቪዬሽን ኢንቨስትመንቶች ላይ በሚያደርገው ተሳትፎ ጠንካራ ክንድነቱን አስመስክሯል። አየር መንገዱ አብዛኛውን የኩባንያዎቹን የባለቤትነት ድርሻና ትርፍ ለባለቤት ሀገራቱ መንግሥታት በመተው፣ የአመራር፣ የስልጠናና የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ የአፍሪካ አቪዬሽን በጋራ እንዲያድግ አድርጓል። በአቪዬሽን እሴት ሰንሰለት (Aviation Value Chain) ውስጥ ያለውን መዋቅራዊ የበላይነት በመጠቀምም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አየር መንገዶች የተቀናጀ የቴክኒክና የስልጠና ድጋፍ ይሰጣል። ተቋሙ በእነዚህ አየር መንገዶች ውስጥ ስትራቴጂካዊ የባለቤትነት ድርሻ በመያዝ፣ አብዛኛውን የኩባንያዎቹን የባለቤትነት መብትና የንግድ ትርፍ ለባለቤት ሀገራቱ መንግሥታት በመተው፣ ሙሉ የኦፕሬሽንና የማኔጅመንት ኃላፊነቱን በመውሰድ አፍሪካውያን ራሳቸውን እንዲችሉ አድርጓል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ አየር መንገዶችን የማቋቋምና የማጠናከር ስራ ሙሉ በሙሉ በፓን አፍሪካዊነት እና በእውነተኛ አፍሪካዊ የትብብር መንፈስ ላይ የተመሠረተ ታላቅ አህጉራዊ ስራ ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚከተለው ሁለገብ ስትራቴጂ ግቡ የገበያ የበላይነትን መቆጣጠር ሳይሆን፣ አቪዬሽን ለሌላቸው ወይም አየር መንገዶቻቸው ለፈረሱባቸው አፍሪካውያን ወንድም ሀገራት የቴክኒክና የአመራር አቅምን ማካፈልም ነው። የአፍሪካ አየር መንገዶችን በጋራ ባለቤትነት ሲያቋቁም የኢኮኖሚ ጥቅሙን ብቻ አስልቶ ሳይሆን፣ በአፍሪካ የነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሠረት የአህጉሪቱን የሰዎችና የዕቃዎች ዝውውርን በማቀላጠፍ የጋራ አፍሪካዊ ብልጽግናን ለማምጣት በማለም ነው። ይህ አካሄድ አህጉሪቱ ከውጭ አየር መንገዶች ጥገኝነት እንድትላቀቅ የሚያደርግ እውነተኛ የፓን አፍሪካዊነት መግለጫ ነው። የራሱን የአብራሪዎች ፣ የኢንጂነሮች እና የበረራ አስተናጋጆችን የሚያሰለጥንበትን ዘመናዊ የአቪዬሽን አካዳሚ በመገንባትም ለአቪዬሽን ዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ ቁልፍ ሚናውን እየተጫወተም ይገኛል። የስልጠና እና የጥገና አቅሙ ከፍተኛ እንደመሆኑም ለተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት የአቪዬሽን ባለሙያዎች ፣ እንዲሁም ከአህጉሪቱ ውጭ ላሉ አየር መንገዶች የስልጠና ፣የጥገና እና የቴክኒክ አገልግሎት በመስጠት የአህጉሪቱ የአቪዬሽን የጀርባ አጥንት መሆኑን አስመስክሯል። ይህ አህጉራዊ ትስስር ሀገራት የየራሳቸውን የአቪዬሽን ዘርፍ እንዲያጠናክሩና በንግድ፣ በቱሪዝም እና በህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ የአፍሪካ ህብረት የአጀንዳ 2063 ራዕይ እንዲሳካ የበኩሉን ሚና ይጫወታል። በየዓመቱ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን የሚያገኘው አየር መንገዱ እንደ ኤይር ባስ ኤ 350-1000 ያሉ ዘመኑን የዋጁ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን በመግዛት በአፍሪካ የመጀመሪያ በመሆን በብቸኝነት የሚያበር ሲሆን በአፍሪካ ትልቁን የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል እና ዘመናዊ የካርጎ (የጭነት) ተቋም በመገንባትም አገልግሎቱን አዘምኗል:: በመላው ዓለም 26 የሚሆኑ ታላላቅ አየር መንገዶች ያሉበት የስታር አሊያንስ አባል በመሆን ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ግዙፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየዓመቱ ለሀገራችን የሚያስገኘው ገቢም ከዋነኛዎቹ የኢኮኖሚ አውታሮች ተርታ ቀዳሚው ያደርገዋል። ዓለምን ያስጨነቀው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በተከሰተበትና ታላላቅ ዓየር መንገዶች በኪሳራ ስራ ባቆሙበት ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለው ቁርጠኝነትና ጠንካራ አመራር አማካኝነት በካርጎ/በጭነት አገልግሎት ለአፍሪካዊያንና ሌሎች የዓለም ሃገራት መድሃኒቶችንና የህክምና መገልገያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ጭነቶችን በማጓጓዝ አለኝታነቱንም ትርፋማነቱንም አረጋግጧል። ለአፍሪካውያን የሚሰራ እውነተኛ አፍሪካዊ ተቋም መሆኑን በተግባር ያረጋገጠው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ዛሬም እንደ ትላንቱ የአህጉሪቱ የልማትና የአንድነት ድልድይ ሆኖ ቀጥሏል። አየር መንገዱ አሁንም የአፍሪካ አዲስ መንፈስ ሆኖ አህጉሪቱን ወደ ላቀ የብልጽግና እና የጋራ የከፍታ ምህዋር መምራቱን በጽናት ይቀጥላል።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 12494
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 22035
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 15069
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20810
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 105426
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79978
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 58326
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55930
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 39951
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 39859
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 39327
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 37808
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 105426
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79978
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 58326
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55930
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ የማዕድን ምርት እመርታ
Aug 21, 2026 805
በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአገር በቀል የኢኮኖሚና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ታግዞ፣ ባለፉት ዓመታት የታዩበትን የአሰራርና መዋቅራዊ ችግሮች በመቅረፍ ከፍተኛ የመነቃቃት ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ዘርፉ በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ ማዕድን በብዝኃ ዘርፍ የልማት ምልከታችን ውስጥ እና በሀገሪቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል። ባለፉት ሶስት አሥርት ዓመታት ውስጥ የማዕድን ዘርፉ ለአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያበረከተው አስተዋጽኦ ከ0 ነጥብ 8 በመቶ በታች የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ግን መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው የላቀ ትኩረት ከፍተኛ መዋቅራዊ ሽግግር እያመጣ ይገኛል። በ2018 በጀት ዓመት ከዘርፉ 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ተችሏል። ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ92 በመቶ የገቢ ዕድገትና የ27 በመቶ የምርት መጠን ብልጫ ያሳየ ሲሆን፣ ምርቶቹም በዋናነት ወደ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ አሜሪካ፣ ጀርመን እና ቻይና ተልከዋል። በወጪ ንግድ እድገት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው የወርቅ ምርት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ለውጭ ገበያ የቀረበ ሲሆን እስከ ዓመቱ ማብቂያ 32 ቶን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።   በባህላዊ መንገድ የሚመረተውን የወርቅ ምርት ለማዘመንም መንግሥት የማጣሪያና ማቀለጫ ፋብሪካዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል። የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ከውጭ የሚገቡ ስትራቴጂክ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህም ለድንጋይ ከሰል ግዢ ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት የተቻለ ሲሆን፣ የሲሚንቶ ምርትም ባለፉት ስምንት ዓመታት ከነበረበት 8 ሚሊየን ቶን አሁን ላይ በዓመት ወደ 14 ሚሊየን ቶን አድጓል። ሀገሪቱ በየዓመቱ ለማዳበሪያ ግዢ የምታወጣውን 2 ቢሊየን ዶላር ለማስቀረትም የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ተጀምሯል። በተጨማሪም በየዓመቱ ለብረት ምርት ግዢ የሚወጣውን 1 ቢሊየን ዶላር በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት የሚያስችል ግዙፍ ፋብሪካ የመገንባት ስምምነት ተፈጽሞ ወደ ስራ ተገብቷል። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በዘርፉ የተሰማሩ ፕሮጀክቶች ዋጋ 10 ቢሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከለውጡ በፊት ከነበረውና ከ100 ሚሊየን ዶላር የማይበልጡ አነስተኛ ኢንቨስትመንቶች በከፍተኛ ደረጃ የለወጠ ስኬት ነው። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በአፋር ክልል የሚገኘውን ግዙፍ የፖታሽ ክምችት ለማልማት ፈቃድ አግኝቶ ወደ ሥራ ገብቷል። በተጨማሪም ታንታለምን እሴት ጨምሮ ለመላክ ከአሜሪካ ኩባንያ ጋር ድርድር እየተደረገ ሲሆን፣ ለባትሪና ቴክኖሎጂ ወሳኝ የሆኑትን ሊቲየም፣ ኮባልትና ኒኬልን ለማምረት ዝግጅት ተጠናቋል። የኢንቨስትመንት ምህዳሩን ሳቢ ለማድረግ የማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ አሰራር ቅድሚያ የመጣን ቅድሚያ ማስተናገድ በሚል መርህ እንዲመራ ተደርጓል። የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና መላኪያ ፈቃዶች፣ እንዲሁም የካዳስተር ሲስተም ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ አሰራር ተሸጋግረዋል። በ2019 በጀት ዓመት ከዘርፉ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፣ የመንግሥት ስትራቴጂካዊ እቅድ እ.አ.አ. በ2030 የማዕድን ወጪ ንግድ ገቢን ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ በማድረስ ኢትዮጵያን ከአፍሪካ አምስት ቀዳሚ የማዕድን አምራች ሀገራት ተርታ ማሰለፍ ነው።   በዘርፉ እየተካሄደ ያለው መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ በውጭ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኝነት በመቀነስ ወደ ኢንዱስትሪ መሪነት የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥነዋል። የወርቅ፣ የተፈጥሮ ጋዝ፣ የፖታሽ እና የቴክኖሎጂ ማዕድናት በሀገር ውስጥ እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ላይ የሚኖራትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ያረጋግጣል።
የአረቡ ዓለም ከግብፅ ምን አተረፈ?
Aug 19, 2026 726
የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ አካሄድ በታሪካዊ እውነታዎች እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ላይ እየተመሠረተ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ ጊዜ ያለፈባቸው የጂኦ ፖለቲካዊ የመጠላለፍ አካሄዶች ዋጋ ቢስነትና ጥቅም አልባነት በግልጽ እየታየ ይገኛል። ለብዙ አስርት ዓመታት ግብፅ የዓረብ ሊግን ለራሷ ጠባብ ፍላጎቶች እና ጂኦፖለቲካዊ አጀንዳዎች ማስፈጸሚያነት በሰፊው ስትጠቀምበት ቆይታለች። ሆኖም ይህ ጥቅምና ጉዳትን ብቻ መሰረት ያደረገ ግንኙነት አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ያስነሳል፦ ለመሆኑ የዓረቡ ዓለም ከግብፅ በምላሹ ያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? ለዚህ ጥያቄ አጭሩ መልስ ምንም የሚል ነው ሲል “What Has the Arab World Gained from Egypt? Why Ethiopia Belongs in the Arab League?” ፀሐፊው እና በፖለቲካና ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ በቋሚነት የሚተነትነው አስተያየት የሚሰጠው ጅብሪል ላሞ በኢዜአ እንግሊዘኛ ገጽ ባሳፈረው ሐተታ ላይ ፣ የግብጽ ፖሊሲዎች እንዲሁም ለሁለት አስርት ዓመታት የዘለቀው አምባገነናዊ አስተዳደር የጋራ ጥንካሬን ከመፍጠር ይልቅ የቀጣናውን አለመረጋጋት ማባባሳቸውን ገልጿል። እነዚህ ፖሊሲዎች፣ በምሥራቅ አፍሪካ እና በቀይ ባሕር አካባቢም ውጥረትን እያባባሱ እንደሚገኙ አመልክቷል። እነዚህ አካባቢዎች ለዓረቡ ዓለም የራቁ አይደሉም፤ ይልቁንም ለዓረቡ ዓለም ደኅንነት፣ የባሕር ንግድ፣ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የምግብ ዋስትና እጅግ ወሳኝ እና ስትራቴጂካዊ ማዕከላት ናቸው። የግብፅ ከፋፋይ ቀጣናዊ አካሄድ ከታዩባቸው ጉልህ ማሳያዎች አንዱ በኤርትራ ጉዳይ እና በሰፊው የኢትዮጵያ ግዛት አንድነት ላይ የነበራት ታሪካዊ ጣልቃ ገብነት ነው። ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ቀጣናዊ ተፅዕኖዋን ለመግታት በግብጽ ታስበው የተደራጁ ተገንጣይ ኃይሎችን እና ፖለቲካዊ ፕሮጀክቶችን በግልጽ ትደግፍ እንደነበረ ፀሐፊው አውስቷል። ከኢትዮጵያ የኤርትራ መገንጠል በምሥራቅ አፍሪካ ቀውስ የተሞላ ታሪክ ውስጥ አቢይ ክስተት ሲሆን፣ የውጭ ጂኦፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነቶች የሀገራትን እጣ ፈንታ እንዴት እንደሚያናጉ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የዲፕሎማሲ ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ የቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ እና የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ፣ ኢትዮጵያን ለማዳከም ታስቦ የተዘረጋውን የኤርትራን የመገንጠል ፕሮጀክት በመደገፍና በማፋጠን ረገድ ትልቅ ሚና ነበራቸው። በተጨማሪም ግብጽ በደቡባዊ የቀይ ባህር ቀጣና የምታካሂደው ቀውስ የመፍጠር እንቅስቃሴ፣ ለዓለም አቀፍ የባህር ንግድና ለቀጣናው ደህንነት ቀጥተኛ ስጋት ደቅኗል። በባብ-ኤል-ማንደብ የባሕር ወሽመጥ አካባቢ ውጥረቶችን በመቀስቀስ እና ተላላኪ ታጣቂ ቡድኖችን በማንቀሳቀስ፣ ወሳኝ የሆኑ የባህር መተላለፊያዎችን የጂኦፖለቲካዊ ግጭት መድረክ አድርጋዋለች። ይህም ለጠቅላላው የዓረብ ዓለም የኢነርጂና የምግብ አቅርቦት መሰረት የሆነውን የደህንነት መዋቅር አደጋ ላይ ጥሎታል፤ ሲሉ ጅብሪል ላሞ ያብራራሉ። ጅብሪል ላሞ በጽሑፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ የግብፅ ግልጽ የራስ ወዳድነት እንቅስቃሴዎች ቀጣናዊ ውጥረትን የሚፈጥሩ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ መቀላቀል ግን ለዓረቡ ዓለም እጅግ ከፍተኛ ጥቅም የሚያስገኝ ለውጥ አምጪ ዕድል ይዞ ይመጣል። በመደመር ፍልስፍና አሳታፊ ማዕቀፍ ሥር፣ ኢትዮጵያ ከማግለል ፖሊሲ ይልቅ የዓረቡን ዓለም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማስተሳሰር የሚያስችል የላቀ የዲፕሎማሲ አቅም አላት። በዚህም የአፍሪካ ዋነኛ የዲፕሎማሲ ማዕከል እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ የባለብዙ ወገን ትብብሮችን በመቅረጽ ረገድ ያላትን የካበተ ልምድ ታካፍላለች። የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ የመቀላቀል ጥረት ጊዜያዊ የፖለቲካ ስሌት ሳይሆን፣ የተፈጥሮ የታሪክ ጥሪ ነው። ከ135 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ፣ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እና ጥልቅ የሥልጣኔ መሠረት ያላት ይህች የቀይ ባሕር ሀገር፣ አባልነቷ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ መካከል ስትራቴጂካዊ ድልድይ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር ያላት ቁርኝት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በጋራ ታሪክ፣ ባህል እና የደም ትስስር ላይ የተገነባ ነው። እንደ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሉ የትምህርት ተቋማት፣ የኢትዮጵያ ጥናቶች በታሪክ ደረጃ ከመካከለኛው እና ከቅርብ ምሥራቅ ታሪክ (Near Eastern Studies) ተመድቦ መጠናቱ፤ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ከቀጣናው ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ ውህደት የሚያረጋግጥ ሕያው ማሳያ ነው። የባብ-ኤል-ማንደብ የባህር ወሽመጥ በጭራሽ መሰናክል አልነበረም፤ ይልቁንም ንግድን፣ ባህልን እና ማህበረሰቦችን በቀይ ባሕር በኩል ያገናኘ ዋንኛ መተላለፊያ ሆኖ አገልግሏል። ከንጉሥ አብረሃ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ በኢትዮጵያውያን እና በመካከለኛው ምሥራቅ ሕዝቦች መካከል የጋራ የደም ትስስር እንደነበር የሚያረጋግጡ ዘመናዊ የስነ ህይወት( ጄኔቲክስ) ጥናቶች፣ የዚህን ታሪካዊ ቁርኝት እውነተኛነት በግልጽ ያሳያሉ። በቋንቋና በባህል ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት መሠረት ታሪካዊ ትስስር ያለው ነው። የሀገሪቱ የቋንቋና የሥነ-ጽሑፍ ውርስ ከዓረብኛ፣ አራማይክና ዕብራይስጥ ጋር በጽኑ የተሳሰረ ሲሆን፣ ይህም በምሥራቅ አፍሪካና በአረቢያ ልሳነ-ምድር መካከል ያለውን ጥልቅ የጋራ የሥልጣኔ ቁርኝት ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ አላት። የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ተስደው በንጉስ ነጃሺ ከለላ ማግኘታቸው የእስልምናን ህልውና የታደገ ታሪካዊ ክስተት ሲሆን፣ ይህም ሀገሪቱን ከዓረቡ ዓለም ጋር በጽኑ አስተሳስሯታል። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ የዓረብ ሊግን በኢትዮጵያ ላይ እንደ ተቋማዊ ተፅዕኖ ማሳደሪያ መሣሪያ ግብጽ ስትጠቀምበት ቆይታለች። ግብፅ የውጭ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ዕድገት፣ የህዳሴውን ግድብም ሆነ የባሕር በር ጥያቄን እንደ ሥጋት በሚያይ ጊዜ ያለፈበት ስሌት ላይ የተመሠረተ ነው። ግብፅ የራሷን የውሃ አቋም በሊጉ ላይ በመጫን፣ ተቋሙ ከኢትዮጵያ ጋር አላስፈላጊ ውጥረት ውስጥ እንዲገባ አድርጋለች። ጅብሪል ላሞ እንዳመለከተው፣ ከግብጽ የአግላይነት ፖሊሲ ይልቅ የዘመኑ ነባራዊ ሁኔታዎች ሙሉ ትብብርን የሚጠይቁ ናቸው። በመደመር መርህ፣ ኢትዮጵያ ለዓረቡ ዓለም ለዘመናት ከቆዩ የጥላቻ መንገዶች በላቀ ሁኔታ የተሻሉ ጥቅሞችን ማቅረብ ትችላለች። እያደገ የመጣው የኢንዱስትሪ እና የአረንጓዴ ኃይል አቅሟ፣ ኢትዮጵያን ለቀይ ባህር ቀጣና የመረጋጋት ምሰሶ አድርጓታል። የመካከለኛው ምሥራቅ ቀጣና የውሃ እጥረት እና የምግብ ዋስትና ሥጋት በተጋረጠበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ የውሃ ሀበት እና ለም መሬት ለቀጣናው ወሳኝ የግብርና-ኢንዱስትሪ አጋር ያደርጋታል። የዓረብ ሊግ አባል ሀገራት የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ብሔረተኝነት በመሻገር፣ የቀይ ባህርን ቀጣና የሥልጣኔ እውነታ መቀበል ይኖርባቸዋል። አረብ ሊግ እንደ ጅቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ኮሞሮስ እና ሞሪታኒያ አባል ሀገራት መያዙ፣ ስብስቡ የተለያዩ ቀጣናዊ እውነታዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑን ያሳያሉ። የዓረብ ሊግ ሙሉ አባልነት የኢትዮጵያን አፍሪካዊ ማንነት ሳይቀንሰው፣ አህጉሩን ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር የሚያገናኝ ዋነኛ ድልድይ የሚያደርጋት በመሆኑ፤ ሊጉ የኢትዮጵያን አጋርነት በመቀበል ለአዲስ አበባ ተገቢውንና ሕጋዊ ቦታዋን የሚሰጥበት ጊዜ አሁን እንደሆነ በመግለጽ ጅብሪል ላሞ ፅሁፉን ቋጭቷል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም