ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የአሜሪካ የቪዛ ዕገዳ በሰሜን ኢትዮጵያ ለተፈጠረው ውጥረት የጽንፈኛው የህወሃት ቡድንን ተጠያቂ ያደረገ ነው
Jun 18, 2026 320
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የተጣለው የአሜሪካ የቪዛ እገዳ በሰሜን ኢትዮጵያ ላለው ውጥረት መባባስ ቀጥተኛ ተጠያቂ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው ሲሉ የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። አቶ ጌታቸው ረዳ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሰጡት ማብራሪያ እገዳው ከዚህ የጥፋት ቡድን ጋር በጥቅምም ሆነ በስትራቴጂ ይተባበራሉ ተብለው ለሚጠረጠሩ እንደ ሻቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት ላሉ የውጭ አካላትም የተላለፈ ግልጽ ማስጠንቀቂያ ነው። የእርምጃው ትልቅነት በቪዛ መከልከሉ ላይ አይደለም፤ ይልቁንም ዋሽንግተን በኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጠረው አዲስ ውጥረት ተጠያቂነቱን ሙሉ በሙሉ በደብረጽዮን ገብረሚካኤል በሚመራው ቡድን ላይ ማድረጉ ነው ሲሉ ተናግረዋል። አቶ ጌታቸው ይህንኑ እርምጃ ሲያብራሩ የቪዛ እገዳው በተለይ ከደብረጽዮን ጋር በቅርብ የሚሰሩ እና በትግራይ ክልል ለሚታየው ቀውስ መባባስ ምክንያት የሆኑ የሕወሃት አክራሪ አባላትን ለይቶ ያነጣጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላምን ለማደፍረስ እና ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሱ በሚገኙ የቀድሞ የህወሓት ጽንፈኛ አመራሮች እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን አስታውቃለች። የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ማዕቀቡ የተጣለው በኢሚግሬሽንና ዜግነት ሕግ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ የቪዛ እገዳ በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን በሚያደናቅፉ፣ ሰላምን በሚያናጉ የሕወሃት ጽንፈኛ አባላትና የቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ ያነጣጠረ ነው። አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይ ክልል ሕዝብን ጨምሮ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን እንደምትቆም አስታውቃለች። በቀጣናው ሰላምና መረጋጋትን አደጋ ላይ የሚጥሉ የሕወሃት ባለሥልጣናትንና ሌሎች ግለሰቦችን ድርጊት ለማጋለጥ እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማስፈን ዋሽንግተን ያሏትን ዲፕሎማሲያዊ አማራጮች በሙሉ መጠቀሟን እንደምትገፋበትም ገልጻለች።
ደቡብ አፍሪካ ከቼክ ሪፐብሊክ ጋር አቻ ተለያይታለች
Jun 18, 2026 163
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ አንድ ሁለተኛ መርሐ ግብር ቼክ ሪፐብሊክ እና ደቡብ አፍሪካ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ማምሻውን በአትላንታ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማይክል ሳዲሌክ በስድስተኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ጎል ቼክ ሪፐብሊክን መሪ አድርጓል። ቴብሆ ሞክዌና በ83ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ባሳረፋት ግብ ደቡብ አፍሪካ አቻ ሆናለች። በጨዋታው ደቡብ አፍሪካ የተሻለ ብልጫ ነበራት። ደቡብ አፍሪካ በዓለም ዋንጫው የመጀመሪያ ነጥቧን አግኝታለች። ቼክ ሪፐብሊክም በተመሳሳይ የመጀመሪያ ነጥቧን አሳክታለች። ደቡብ አፍሪካ ወደ ጥሎ ማለፉ የመግባት ተስፋዋን ለማለምለም በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኮሪያ ሪፐብሊክን ማሸነፍ ይኖርባታል። በዚሁ ምድብ ሜክሲኮ ከኮሪያ ሪፐብሊክ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በጓድላሃራ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሁለቱ ሀገራት የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸውን ማሸነፋቸው የሚታወቅ ሲሆን አሸናፊው ቡድን ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ያረጋግጣል።
በፌዴራል ዋና ኦዲተር የኦዲት ሽፋን፣ ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች የሚበረታቱ ናቸው 
Jun 18, 2026 176
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- የፌዴራል ዋና ኦዲተር የኦዲት ሽፋንን ጥራትና ተደራሽነት ለማሳደግ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን የሕዝብ ተወካዮች የምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ26ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የፌዴራል ዋና ኦዲተር ያቀረበውን የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የፋይናንሺያል፣ የሕጋዊነት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ላይ ተወያይቷል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ሪፖርቱን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። ዋና ኦዲተሯ በሪፖርታቸው፤ በተቋማት በጀት አጠቃቀም፣ በተሰብሳቢ ሒሳብ መጠን እንዲሁም በፕሮጀክቶች ውል መቋረጥ ላይ መሻሻሎች መታየታቸውን አንስተዋል።   የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ የፌዴራል ዋና ኦዲተር የኦዲት ሽፋን ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ እያከናወናቸው የሚገኙት ሥራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በየዓመቱ የሚቋረጡ ፕሮጀክቶች ቁጥር እያነሰ መምጣቱን ሪፖርቱ የሚያመላክት መሆኑን ያነሱት የምክር ቤት አባላቱ፤ የኦዲት ጥራትንና ግልጽነትን ለማጠናከር በፌዴራል ዋና ኦዲተር በኩል እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችንም አድንቀዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ በበኩላቸው፤ የኦዲት ጥራትን ለማሻሻል በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞም የተቋማትን የውስጥ ኦዲት ጥራት የሚያሻሽሉ የአቅም ግንባታ ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ዋና ኦዲተሯ አስረድተዋል። የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር)፤ በ2017 በጀት ዓመት ለልማት ሥራዎች ከተመደበው በጀት ውስጥ የዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የ99 ነጥብ 3 በመቶ የኦዲት ሽፋን ማሳካት መቻሉን አስታውቀዋል።   በተጨማሪም የክዋኔ ኦዲት ትግበራ በየዓመቱ እያደገ መምጣቱ የተቋሙን የኦዲት አቅም ውጤታማነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ አክለውም፤ በየበጀት ዓመቱ በምክር ቤቱ የሚጸድቀው የኦዲት ሽፋን ሙሉ በሙሉ እንዲካሄድና ለክዋኔ ኦዲትም በቂ ሽፋን እንዲኖር ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ ይገባቸዋል ብለዋል። የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፤ የፌዴራል ዋና ኦዲተር ተወዳዳሪና ጠንካራ አሠራርን ለማጎልበት እያከናወናቸው የሚገኙት ተግባራት የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ምክትል አፈ ጉባኤዋ በየዓመቱ እየተገኙ ያሉ ለውጦችን ይበልጥ በማሳደግ እንዲሁም የታዩ ውስንነቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የቅንጅት ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ በርካታ ስደተኞችን በማስተናገድ የአፍሪካውያንን የጋራ መረዳዳት እሴት በተግባር እያሳየች ነው
Jun 18, 2026 224
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ በርካታ ስደተኞችን በማስተናገድ የአፍሪካውያንን የጋራ መረዳዳት እሴት በተግባር እያሳየች መሆኗን የአፍሪካ ሕብረት የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ ገለጹ። የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ስደተኞች በመጠለያ ጣቢያዎች ያላቸውን ሕይወት ከሀገራዊ ሥርዓቶች ጋር ማስተሳሰርን ማዕከል ያደረገ አዲስ የማካተት ፍኖተ-ካርታ ይፋ አድርጓል፡፡   የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ከቀጣናው በሙሉ ለሚመጡ ስደተኞች የምታሳየውን የረጅም ጊዜ የእንግዳ ተቀባይነት ባህልና አጋርነት ሕብረቱ ትልቅ ግምት እንደሚሰጠው ገልጸዋል። ባለፉት በርካታ አሥርት ዓመታት ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞችን ከለላ በመስጠት ለአፍሪካውያን ኩራት የሆነውን የጋራ መረዳዳትና ኃላፊነትን በተግባር ማሳየቷን ጠቁመዋል። አዲሱ የማካተት ፍኖተ-ካርታ በዚህ ኩሩ ታሪካዊ ቅርስ ላይ የተገነባ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በጠንካራ አጋርነት እና ቀጣይነት ባለው የፖለቲካ ቁርጠኝነት የተደገፈ ሀገራዊ አመራር የተገኘ ትልቅ ውጤት መሆኑን አብራርተዋል። ፍኖተ-ካርታው ስደተኞች እና አስተናጋጁ ማኅበረሰብ በጋራ ሊበለጽጉና ሊያድጉ የሚችሉባቸውን አዳዲስ ዕድሎች የሚያሳይ መሆኑንም አክለዋል።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ምክትል ዋና ጸሐፊ መሀመድ አብዲ ዋሬ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ተራማጅና አካታች የሆኑ የስደተኞች ፖሊሲዎችን በማውጣትና በማሳደግ ረገድ ለአፍሪካ በአርአያነት የምትጠቀስ ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። አሁን ይፋ የሆነው የማካተት ፍኖተ-ካርታ የዘመናችንን እጅግ አጣዳፊና ውስብስብ የስደተኞች ፈተናዎች ለመፍታት ኢትዮጵያ ያላትን ግልጽ ራዕይና የማይናወጥ ቁርጠኝነት በአጽንኦት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትርክት ግንባታ ያላትን የመሪነት ሚና አጠናክራ ትቀጥላለች
Jun 18, 2026 215
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትርክት ግንባታ ላይ ያላትን ቀዳሚና የመሪነት ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ በስኬት እንዲካሄድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል፡፡   በዚሁ የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ፣ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ከተለያዩ ተቋማት የተወጣጡ ተወካዮችና የክብር እንግዶች ተገኝተዋል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና በኤ.ጂ.ኤ.ቴክ ኢንተርፕራይዝ ትብብር በአዲስ አበባ ከተማ መካሄዱ ይታወቃል። ሚያዚያ 29 እና ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደው በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ተሳትፈዋል። ተሳታፊዎቹ በአዲስ አበባና በተለያዩ የሀገሪቷ ክልሎች የተከናወኑ ታላላቅ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።   ጉባዔው የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና የዲጂታል ትርክቱን አህጉሪቱ እራሷ በባለቤትነት እንድትመራው ያለመ ሲሆን፤ እቅዱንና ዓላማውን ሙሉ በሙሉ ያሳካ ውጤታማ መድረክ ሆኖ ተጠናቋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የቦርድ ሰብሳቢ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ትርክት መገንባት ለአጠቃላይ የአፍሪካ ትርክት ግንባታ ወሳኝ መሰረት ነው። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ስኬቶች በስፋት መነገር መጀመራቸው አፍሪካ ቀና እንድትል እያደረጋት ከመሆኑም በላይ፤ መሬት ላይ ያለውን እውነታ ለዓለም ማስተዋወቅ ተችሏል ብለዋል። ስለ ኢትዮጵያና አፍሪካ ትክክለኛውን ታሪክና እውነታ ለዓለም ማሳወቅ ብሎም ከዚህ ቀደም የተፈጠሩ አፍራሽ ግንዛቤዎችን ለመቀየር ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን የሚጫወቱትን ሚና ከመቼውም ጊዜ በላይ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡ ፡ ጉባኤው ሊጠናከር የሚገባው በጎ ጅምር መሆኑን በመጥቀስም ለስኬቱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።   የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጉባኤው የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ በገነባ መልኩ እጅግ ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በቅንጅት የተሰራው ስራ ለውጤታማነቱ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመው፤ የቱሪዝም ሚኒስቴር መሰል አህጉራዊ ፋይዳ ያላቸው ታላላቅ ጉባኤዎች በቀጣይም በተጠናከረ መልኩ እንዲካሄዱ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሁሉ እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ በጉባኤው ላይ በድምሩ ከ480 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያላቸው 200 የሀገር ውስጥና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሳተፋቸውን ተናግረዋል፡፡   መድረኩ ኢትዮጵያ በልማት ዘርፍና ለአፍሪካ ገጽታ ግንባታ ምን ያህል ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነች እንደሆነ ማሳየት የተቻለበት መሆኑን ጠቁመው፤ የሀገሪቷን የቱሪዝም ሀብቶች ለማስተዋወቅ የረዳ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ጠቅሰዋል። የኤ ጂ ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር አብዲ ጠና በበኩላቸው፤ ጉባኤው በአፍሪካ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች እርስ በእርስ እንዲተዋወቁና ለጋራ ዓላማ አብረው እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በንግግራቸው አንስተዋል።
የሚታይ
የአሜሪካ የቪዛ ዕገዳ በሰሜን ኢትዮጵያ ለተፈጠረው ውጥረት የጽንፈኛው የህወሃት ቡድንን ተጠያቂ ያደረገ ነው
Jun 18, 2026 320
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የተጣለው የአሜሪካ የቪዛ እገዳ በሰሜን ኢትዮጵያ ላለው ውጥረት መባባስ ቀጥተኛ ተጠያቂ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው ሲሉ የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። አቶ ጌታቸው ረዳ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሰጡት ማብራሪያ እገዳው ከዚህ የጥፋት ቡድን ጋር በጥቅምም ሆነ በስትራቴጂ ይተባበራሉ ተብለው ለሚጠረጠሩ እንደ ሻቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት ላሉ የውጭ አካላትም የተላለፈ ግልጽ ማስጠንቀቂያ ነው። የእርምጃው ትልቅነት በቪዛ መከልከሉ ላይ አይደለም፤ ይልቁንም ዋሽንግተን በኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጠረው አዲስ ውጥረት ተጠያቂነቱን ሙሉ በሙሉ በደብረጽዮን ገብረሚካኤል በሚመራው ቡድን ላይ ማድረጉ ነው ሲሉ ተናግረዋል። አቶ ጌታቸው ይህንኑ እርምጃ ሲያብራሩ የቪዛ እገዳው በተለይ ከደብረጽዮን ጋር በቅርብ የሚሰሩ እና በትግራይ ክልል ለሚታየው ቀውስ መባባስ ምክንያት የሆኑ የሕወሃት አክራሪ አባላትን ለይቶ ያነጣጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላምን ለማደፍረስ እና ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሱ በሚገኙ የቀድሞ የህወሓት ጽንፈኛ አመራሮች እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን አስታውቃለች። የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ማዕቀቡ የተጣለው በኢሚግሬሽንና ዜግነት ሕግ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ የቪዛ እገዳ በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን በሚያደናቅፉ፣ ሰላምን በሚያናጉ የሕወሃት ጽንፈኛ አባላትና የቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ ያነጣጠረ ነው። አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይ ክልል ሕዝብን ጨምሮ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን እንደምትቆም አስታውቃለች። በቀጣናው ሰላምና መረጋጋትን አደጋ ላይ የሚጥሉ የሕወሃት ባለሥልጣናትንና ሌሎች ግለሰቦችን ድርጊት ለማጋለጥ እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማስፈን ዋሽንግተን ያሏትን ዲፕሎማሲያዊ አማራጮች በሙሉ መጠቀሟን እንደምትገፋበትም ገልጻለች።
ኢትዮጵያ በርካታ ስደተኞችን በማስተናገድ የአፍሪካውያንን የጋራ መረዳዳት እሴት በተግባር እያሳየች ነው
Jun 18, 2026 224
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ በርካታ ስደተኞችን በማስተናገድ የአፍሪካውያንን የጋራ መረዳዳት እሴት በተግባር እያሳየች መሆኗን የአፍሪካ ሕብረት የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ ገለጹ። የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ስደተኞች በመጠለያ ጣቢያዎች ያላቸውን ሕይወት ከሀገራዊ ሥርዓቶች ጋር ማስተሳሰርን ማዕከል ያደረገ አዲስ የማካተት ፍኖተ-ካርታ ይፋ አድርጓል፡፡   የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ከቀጣናው በሙሉ ለሚመጡ ስደተኞች የምታሳየውን የረጅም ጊዜ የእንግዳ ተቀባይነት ባህልና አጋርነት ሕብረቱ ትልቅ ግምት እንደሚሰጠው ገልጸዋል። ባለፉት በርካታ አሥርት ዓመታት ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞችን ከለላ በመስጠት ለአፍሪካውያን ኩራት የሆነውን የጋራ መረዳዳትና ኃላፊነትን በተግባር ማሳየቷን ጠቁመዋል። አዲሱ የማካተት ፍኖተ-ካርታ በዚህ ኩሩ ታሪካዊ ቅርስ ላይ የተገነባ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በጠንካራ አጋርነት እና ቀጣይነት ባለው የፖለቲካ ቁርጠኝነት የተደገፈ ሀገራዊ አመራር የተገኘ ትልቅ ውጤት መሆኑን አብራርተዋል። ፍኖተ-ካርታው ስደተኞች እና አስተናጋጁ ማኅበረሰብ በጋራ ሊበለጽጉና ሊያድጉ የሚችሉባቸውን አዳዲስ ዕድሎች የሚያሳይ መሆኑንም አክለዋል።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ምክትል ዋና ጸሐፊ መሀመድ አብዲ ዋሬ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ተራማጅና አካታች የሆኑ የስደተኞች ፖሊሲዎችን በማውጣትና በማሳደግ ረገድ ለአፍሪካ በአርአያነት የምትጠቀስ ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። አሁን ይፋ የሆነው የማካተት ፍኖተ-ካርታ የዘመናችንን እጅግ አጣዳፊና ውስብስብ የስደተኞች ፈተናዎች ለመፍታት ኢትዮጵያ ያላትን ግልጽ ራዕይና የማይናወጥ ቁርጠኝነት በአጽንኦት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትርክት ግንባታ ያላትን የመሪነት ሚና አጠናክራ ትቀጥላለች
Jun 18, 2026 215
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትርክት ግንባታ ላይ ያላትን ቀዳሚና የመሪነት ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ በስኬት እንዲካሄድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል፡፡   በዚሁ የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ፣ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ከተለያዩ ተቋማት የተወጣጡ ተወካዮችና የክብር እንግዶች ተገኝተዋል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና በኤ.ጂ.ኤ.ቴክ ኢንተርፕራይዝ ትብብር በአዲስ አበባ ከተማ መካሄዱ ይታወቃል። ሚያዚያ 29 እና ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደው በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ተሳትፈዋል። ተሳታፊዎቹ በአዲስ አበባና በተለያዩ የሀገሪቷ ክልሎች የተከናወኑ ታላላቅ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።   ጉባዔው የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና የዲጂታል ትርክቱን አህጉሪቱ እራሷ በባለቤትነት እንድትመራው ያለመ ሲሆን፤ እቅዱንና ዓላማውን ሙሉ በሙሉ ያሳካ ውጤታማ መድረክ ሆኖ ተጠናቋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የቦርድ ሰብሳቢ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ትርክት መገንባት ለአጠቃላይ የአፍሪካ ትርክት ግንባታ ወሳኝ መሰረት ነው። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ስኬቶች በስፋት መነገር መጀመራቸው አፍሪካ ቀና እንድትል እያደረጋት ከመሆኑም በላይ፤ መሬት ላይ ያለውን እውነታ ለዓለም ማስተዋወቅ ተችሏል ብለዋል። ስለ ኢትዮጵያና አፍሪካ ትክክለኛውን ታሪክና እውነታ ለዓለም ማሳወቅ ብሎም ከዚህ ቀደም የተፈጠሩ አፍራሽ ግንዛቤዎችን ለመቀየር ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን የሚጫወቱትን ሚና ከመቼውም ጊዜ በላይ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡ ፡ ጉባኤው ሊጠናከር የሚገባው በጎ ጅምር መሆኑን በመጥቀስም ለስኬቱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።   የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጉባኤው የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ በገነባ መልኩ እጅግ ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በቅንጅት የተሰራው ስራ ለውጤታማነቱ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመው፤ የቱሪዝም ሚኒስቴር መሰል አህጉራዊ ፋይዳ ያላቸው ታላላቅ ጉባኤዎች በቀጣይም በተጠናከረ መልኩ እንዲካሄዱ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሁሉ እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ በጉባኤው ላይ በድምሩ ከ480 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያላቸው 200 የሀገር ውስጥና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሳተፋቸውን ተናግረዋል፡፡   መድረኩ ኢትዮጵያ በልማት ዘርፍና ለአፍሪካ ገጽታ ግንባታ ምን ያህል ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነች እንደሆነ ማሳየት የተቻለበት መሆኑን ጠቁመው፤ የሀገሪቷን የቱሪዝም ሀብቶች ለማስተዋወቅ የረዳ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ጠቅሰዋል። የኤ ጂ ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር አብዲ ጠና በበኩላቸው፤ ጉባኤው በአፍሪካ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች እርስ በእርስ እንዲተዋወቁና ለጋራ ዓላማ አብረው እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በንግግራቸው አንስተዋል።
ከጎሮ እስከ ኮዬ ፈጬ አደባባይ ያለው አዲስ የኮሪደር ልማት ስራ ተጀመረ
Jun 18, 2026 184
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከጎሮ እስከ ኮዬ ፈጬ አደባባይ ድረስ ያለውን አዲስ የኮሪደር ልማት ስራ በተቀናጀና በተደራጀ አግባብ መጀመሩን አስታወቁ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመልእክታቸው፤ ከጎሮ መታጠፊያ እስከ ኮዬ ፈጬ አደባባይ ያስጀመርነው የኮሪደር ልማት አጠቃላይ የመንገዱ ርዝመት 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ሲሆን፣ የመንገዱ ስፋት 70 ሜትር (ስምንት ሌን ያለው) ሆኖ ከነግሪነሪው 124 ሜትር ስፋት እንደሚኖረው ገልጸዋል።   ከዚህም በተጨማሪ 21 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የሳይክል መንገድ፣ 21 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና በሁለቱም በኩል 4.5 ሜትር ስፋት ያለው የእግረኛ መንገድ፣ ሰፊ የአረንጓዴ ሽፋን እንዲሁም የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ በውስጡ እንደሚኖረው አመልክተዋል። ይህ የኮሪደር ልማት በከተማዋ ቀደም ሲል የለሙ መሰረተ ልማቶችን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያስተሳስር፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን የሚያነቃቃ እና በመንገዱ ላይ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ የሚፈታ መሆኑን አመልክተዋል። መነሻውን ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር ያደረገ በመሆኑም ሀገራዊ ሁነቶችን ለማስተናገድ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥርና የአካባቢውን ስታንዳርድ በእጅጉ በሚያሳድግ ሁኔታ እንደሚሰራም ነው ያብራሩት።   በኮሪደሩ ላይ ሞሎች፣ የቢዝነስ ተቋማት እና ሌሎች ኮሚኒቲዎች እንደሚገነቡ ገልጸው ከዚህ ቀደም በመንገዱ ዙሪያ ከደረጃ በታች ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን ከፍ ባለ ደረጃ ለመስጠት በሚያስችል መልኩ በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትልቅ ርብርብ እንደሚሰራም ከንቲባዋ ጠቁመዋል። ይህ ኮሪደር ከከተመዋ አልፎ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው፣ ለአካባቢው ነዋሪ ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር፣ አካባቢውን ወደ ትልቅ የንግድ እንቅስቃሴ የሚቀይር ነው ብለዋል። በአካባቢው ላይ የሚኖሩ የከተማዋ ነዋሪዎች ትብብራቸው እንደ ወትሮው የተጠናከረ እንዲሆንና አብረን እንድንሰራ፤ እንዲሁም በስራው ውስጥ የሚሳተፉ ኮንትራክተሮች፣ ማህበራት፣ አማካሪዎች በአጠቃላይ ባለድርሻ አካላት በትብብር በፍጥነት በጋራ እንዲሳካ ከንቲባዋ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከባንዳና ከባዕዳን ኃይሎች ጋር በመቀናጀት ግጭት ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ይገኛል
Jun 18, 2026 281
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከፈጸመው ግፍ ተጠያቂነት ለማምለጥ ከውስጥና ከውጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በመሻረክ ግጭት ለመፍጠርና በሁከት ለመኖር መወሰኑን በተግባር እያሳየ መሆኑን የስምረት ፓርቲ የምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ምክትል ኃላፊ ጠዓመ ዓረዶም ገለጹ። የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ጠዓመ ዓረዶም በትግራይ ክልል ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊ በሆነበት ወቅት በክልሉ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የፈጠረ መሆኑን ገልጸው፤ በስምምነቱ መሠረት የፌዴራል መንግሥት ተቋርጠው የቆዩትን የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በአፋጣኝ ወደ ሥራ እንዲመለሱ ማድረጉን አንስተዋል። በጦርነቱ ተሳታፊ የነበሩ ወጣቶችን በመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም አማካኝነት ወደ ቀድሞ ኑሯቸውና ሥራቸው እንዲመለሱ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በፌዴራል መንግሥቱ የበጀት ድጋፍም ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው የቀድሞው የሕወሃት ቡድን በህገ ወጥና እኩይ ተግባራት ላይ መሰማራቱን አንስተው፥የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለዳግም ጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል ብለዋል። በዚህም በስምምነቱ መሠረት የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስና ፕሬዚዳንቱን በኃይል ከሥልጣን በማውረድ፣ በህገ ወጥ ምርጫ የተሰየመውን የቀድሞውን ምክር ቤት ወደ ስራ በመመለስ አዲስ ካቢኔ ማዋቀሩን ጠቁመዋል። ቡድኑ ከፌዴራል መንግሥት የሚመደበውን የልማት በጀት ራሱን ለዕኩይ ተግባር መልሶ ለማደራጀት እየተጠቀመበት እንደሚገኝ ነው አቶ ጣዕመ የገለጹት። ይህንን የቡድኑን ሕገ-ወጥ አካሄድ የሚቃወሙ የትግራይ ነዋሪዎችን በማሰርና በማንገላታት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከተጠያቂነት ለማምለጥ ሲል ከውስጥና ከውጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር፣ ክልሉን በሁከትና ብጥብጥ ውስጥ ለማቆየት መወሰኑን በተግባር እያሳየ መሆኑን አስታውቀዋል። የቀድሞ ህወሃት በክልሉ ዳግም የጦርነት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ፓርቲያቸው ባደረገው ዳሰሳ ማረጋገጡን የገለጹት አቶ ጠዓመ፣በርካታ ወጣቶች ያለ ፍላጎታቸው በሌሊት እየታፈሱ ወደ ጦር ካምፕ እየተወሰዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተጨማሪም ቡድኑ ወጣቶችን ለወታደራዊ ሥልጠና ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በአስገዳጅ ሁኔታ በመላክና ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመስራት፣ ሊቀሰቅስ ያሰበውን ጦርነት ቀጣናዊ መልክ ለማስያዝ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከሀገር ውስጥ ተስፋ ከቆረጡና ከውጭ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ከሚቃወሙ አካላት ጋር "ፅምዶ" የተሰኘ ጸረ ሰላም ጥምረት በመፍጠር ሀገር ለማተራመስ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብና በቀይ ባሕር ጥያቄ ዙሪያ ያገኘችውን ዲፕሎማሲያዊ ተቀባይነት ለማጠልሸት ቡድኑ ከውስጥ ባንዳና ከውጭ ባዕድ ኃይሎች ጋር በቅንጅት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የአሜሪካ የቪዛ ዕገዳ በሰሜን ኢትዮጵያ ለተፈጠረው ውጥረት የጽንፈኛው የህወሃት ቡድንን ተጠያቂ ያደረገ ነው
Jun 18, 2026 320
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የተጣለው የአሜሪካ የቪዛ እገዳ በሰሜን ኢትዮጵያ ላለው ውጥረት መባባስ ቀጥተኛ ተጠያቂ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው ሲሉ የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። አቶ ጌታቸው ረዳ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሰጡት ማብራሪያ እገዳው ከዚህ የጥፋት ቡድን ጋር በጥቅምም ሆነ በስትራቴጂ ይተባበራሉ ተብለው ለሚጠረጠሩ እንደ ሻቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት ላሉ የውጭ አካላትም የተላለፈ ግልጽ ማስጠንቀቂያ ነው። የእርምጃው ትልቅነት በቪዛ መከልከሉ ላይ አይደለም፤ ይልቁንም ዋሽንግተን በኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጠረው አዲስ ውጥረት ተጠያቂነቱን ሙሉ በሙሉ በደብረጽዮን ገብረሚካኤል በሚመራው ቡድን ላይ ማድረጉ ነው ሲሉ ተናግረዋል። አቶ ጌታቸው ይህንኑ እርምጃ ሲያብራሩ የቪዛ እገዳው በተለይ ከደብረጽዮን ጋር በቅርብ የሚሰሩ እና በትግራይ ክልል ለሚታየው ቀውስ መባባስ ምክንያት የሆኑ የሕወሃት አክራሪ አባላትን ለይቶ ያነጣጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላምን ለማደፍረስ እና ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሱ በሚገኙ የቀድሞ የህወሓት ጽንፈኛ አመራሮች እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን አስታውቃለች። የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ማዕቀቡ የተጣለው በኢሚግሬሽንና ዜግነት ሕግ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ የቪዛ እገዳ በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን በሚያደናቅፉ፣ ሰላምን በሚያናጉ የሕወሃት ጽንፈኛ አባላትና የቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ ያነጣጠረ ነው። አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይ ክልል ሕዝብን ጨምሮ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን እንደምትቆም አስታውቃለች። በቀጣናው ሰላምና መረጋጋትን አደጋ ላይ የሚጥሉ የሕወሃት ባለሥልጣናትንና ሌሎች ግለሰቦችን ድርጊት ለማጋለጥ እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማስፈን ዋሽንግተን ያሏትን ዲፕሎማሲያዊ አማራጮች በሙሉ መጠቀሟን እንደምትገፋበትም ገልጻለች።
የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከባንዳና ከባዕዳን ኃይሎች ጋር በመቀናጀት ግጭት ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ይገኛል
Jun 18, 2026 281
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከፈጸመው ግፍ ተጠያቂነት ለማምለጥ ከውስጥና ከውጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በመሻረክ ግጭት ለመፍጠርና በሁከት ለመኖር መወሰኑን በተግባር እያሳየ መሆኑን የስምረት ፓርቲ የምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ምክትል ኃላፊ ጠዓመ ዓረዶም ገለጹ። የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ጠዓመ ዓረዶም በትግራይ ክልል ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊ በሆነበት ወቅት በክልሉ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የፈጠረ መሆኑን ገልጸው፤ በስምምነቱ መሠረት የፌዴራል መንግሥት ተቋርጠው የቆዩትን የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በአፋጣኝ ወደ ሥራ እንዲመለሱ ማድረጉን አንስተዋል። በጦርነቱ ተሳታፊ የነበሩ ወጣቶችን በመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም አማካኝነት ወደ ቀድሞ ኑሯቸውና ሥራቸው እንዲመለሱ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በፌዴራል መንግሥቱ የበጀት ድጋፍም ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው የቀድሞው የሕወሃት ቡድን በህገ ወጥና እኩይ ተግባራት ላይ መሰማራቱን አንስተው፥የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለዳግም ጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል ብለዋል። በዚህም በስምምነቱ መሠረት የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስና ፕሬዚዳንቱን በኃይል ከሥልጣን በማውረድ፣ በህገ ወጥ ምርጫ የተሰየመውን የቀድሞውን ምክር ቤት ወደ ስራ በመመለስ አዲስ ካቢኔ ማዋቀሩን ጠቁመዋል። ቡድኑ ከፌዴራል መንግሥት የሚመደበውን የልማት በጀት ራሱን ለዕኩይ ተግባር መልሶ ለማደራጀት እየተጠቀመበት እንደሚገኝ ነው አቶ ጣዕመ የገለጹት። ይህንን የቡድኑን ሕገ-ወጥ አካሄድ የሚቃወሙ የትግራይ ነዋሪዎችን በማሰርና በማንገላታት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከተጠያቂነት ለማምለጥ ሲል ከውስጥና ከውጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር፣ ክልሉን በሁከትና ብጥብጥ ውስጥ ለማቆየት መወሰኑን በተግባር እያሳየ መሆኑን አስታውቀዋል። የቀድሞ ህወሃት በክልሉ ዳግም የጦርነት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ፓርቲያቸው ባደረገው ዳሰሳ ማረጋገጡን የገለጹት አቶ ጠዓመ፣በርካታ ወጣቶች ያለ ፍላጎታቸው በሌሊት እየታፈሱ ወደ ጦር ካምፕ እየተወሰዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተጨማሪም ቡድኑ ወጣቶችን ለወታደራዊ ሥልጠና ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በአስገዳጅ ሁኔታ በመላክና ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመስራት፣ ሊቀሰቅስ ያሰበውን ጦርነት ቀጣናዊ መልክ ለማስያዝ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከሀገር ውስጥ ተስፋ ከቆረጡና ከውጭ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ከሚቃወሙ አካላት ጋር "ፅምዶ" የተሰኘ ጸረ ሰላም ጥምረት በመፍጠር ሀገር ለማተራመስ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብና በቀይ ባሕር ጥያቄ ዙሪያ ያገኘችውን ዲፕሎማሲያዊ ተቀባይነት ለማጠልሸት ቡድኑ ከውስጥ ባንዳና ከውጭ ባዕድ ኃይሎች ጋር በቅንጅት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
አሜሪካ በቀድሞው የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች ላይ የወሰደችው እርምጃ የቡድኑን አፍራሽ አካሄድ ለዓለም ያጋለጠ ነው
Jun 18, 2026 295
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- አሜሪካ በቀድሞው የሕወሓት ጽንፈኛ የቡድኑ አመራሮች እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የጣለችው የቪዛ እገዳ፣ የቡድኑን ጽንፈኝነትና አፍራሽ አካሄድ ለዓለም ማኅበረሰብ ያጋለጠ ነው ሲሉ የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ጠዓመ ዓረዶም ገለጹ። አሜሪካ በቀድሞው የሕወሓት ጽንፈኛ አመራሮች እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን መግለጿ ይታወቃል፡፡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ እንደገለጸው፤ የቪዛ እገዳ የተጣለው የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ ተሳታፊ ናቸው በተባሉ አክራሪ የህወሓት አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ ነው፡፡ የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ጠዓመ ዓረዶም ውሳኔውን አስመልክተው ለኢዜአ እንደገለጹት፣ እርምጃው የአሜሪካ መንግስት የቀድሞው ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን በትግራይ ክልል ውስጥ እያደረገ ያለውን የጦርነት ትንኮሳና የሰላም ስምምነቱን የማፍረስ ሴራ በተገቢው መንገድ የተረዳ መሆኑን የሚያሳይ ነው። አሜሪካ የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ በቅርበት ስትከታተል እንደነበረችም ውሳኔው ማረጋገጫ ነው ሲሉ አክለዋል። ጽንፈኛው ቡድን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ በማፍረስ ጊዜው ያለፈበትንና የፈረሰውን ምክር ቤት በድጋሚ በማዋቀር የራሱን ፕሬዝዳንትና አዲስ ካቢኔ መምረጡ ለግጭትና ሁከት መዘጋጀቱን ያሳያል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ጽንፈኛ ቡድኑ ሰፊ ወታደራዊ ዝግጅትና የጦርነት ትንኮሳዎችን እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ ስለሆነም አሜሪካ በዚህ ወቅት የወሰደችው እርምጃ ለሰላም ፈላጊዎች ትልቅ የምስራች መሆኑን ጠቁመው፤በትግራይ ህዝብ ላይ የሰላም እጦትና ጦርነት የሚደግሰውን ቡድን ለይቶ የመታ ነው ብለዋል። አሁን የተወሰደው እርምጃ የሁሉም የትግራይ ሰላምና የለውጥ ፈላጊ ኃይሎችና የፓርቲያቸው ትግል ያመጣው ውጤት መሆኑን ጠቅሰው፣ሆኖም ግን እርምጃው ከዚህ በላይ ሊጠነክር እንደሚገባ አመልክተዋል። ቡድኑ እስካሁን እያደረገ ያለው ተግባር ግልጽ የአሸባሪነት ስራ ነው ያሉት አቶ ጠዓመ፤ ልክ እንደ ሌሎች ዓለም አቀፍ አሸባሪዎች ሁሉ ይህ ቡድንም በአሜሪካ መንግስትና በዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ዘንድ በልዩ ሁኔታ በአሸባሪነት ሊፈረጅ ይገባል ብለዋል፡፡ የቡድኑን አጥፊ እንቅስቃሴ የዓለም ማኅበረሰብ በሚገባ እንዲገነዘበው ፓርቲያቸው ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የፌዴራል መንግስትም ሕገ-መንግስታዊ ኃላፊነቱን በመጠቀም የቀድሞው ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን ላይ ሕግ የማስከበር ስራውን እንዲወጣ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በምክክር ሂደቱ የታየውን ጠንካራ ትብብርና ተሳትፎ በማስቀጠል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት መቋጨት ይገባል
Jun 18, 2026 231
ሀዋሳ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- በምክክር ሂደቱ የታየውን ጠንካራ ትብብርና ተሳትፎ በማስቀጠል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት መቋጨት እንደሚገባ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፣ ከቀናት በፊት በሰጡት መግለጫ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ላለፉት አራት አመታት አካታች፣ አሳታፊና ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ መዝለቁን አስታውሰዋል፡፡ ከዚህ በመቀጠል ዋናውን የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ገልጸው በዚሁ መሰረት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚካሄድ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የምክክር ሂደቱ ቀጥሎ ዋናው የምክክር ጉባኤ በስኬት እንዲቋጭ የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎ፣ ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን በምክክር ሂደቱ እስካሁን የታየውን የስኬት ጉዞ በማስቀጠል ፍፃሜውን ለሚፈለገው ውጤት ለማብቃት የሁላችንም ትጋት ያስፈልጋል ብለዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ የሥነጽሁፍ መምህር አምሳሌ ሀጥዬ፤ በምክክር ሂደቱ የኮሚሽኑ ብርቱ ጥረትና አጠቃላይ የህዝቡ ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። ምክክሩ የቆዩ ችግሮችን በመፍታት ህብረ ብሄራዊ ሀገራዊ አንድነትን ለማጽናትና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ቁልፍ አበርክቶ የሚኖረው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የታየውን ጠንካራ ትብብርና ተሳትፎ በማስቀጠል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት መቋጨት ይገባል ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የህግና ገቨርናንስ ኮሌጅ መምህር ብሩክ ደስታ፤ የምክክር ሂደቱ ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ በታሪክ አጋጣሚ የተፈጠረ መልካም እድል መሆኑን ገልጸዋል። የእስካሁኑ ሂደት በብዙ መልኩ ዜጎች የተሳተፉበትና የአጀንዳ ማሰባሰቡም ከሁሉም አቅጣጫዎች አካታች በሆነ መልኩ የተካሄደ መሆኑን ተገንዝበናል ብለዋል። በታሪክ አጋጣሚ የተገኘውን ይህንን መልካም እድል በአግባቡ በመጠቀም ለሀገራዊ ችግሮች በምክክር መፈትሄ አበጅቶ መቋጨት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የታየውን የዜጎች ጠንካራ ትብብርና ተሳትፎ በማስቀጠል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ማጠናቀቅ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በዩኒቨርስቲው የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር)፤ በምክክሩ የእስካሁኑ ሂደት የሁሉም ትብብርና ተሳትፎ በጉልህ የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በመጨረሻ የሚፈለገው ውጤት እንዲመጣ መትጋት ለስኬታማነቱም መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መግለጹ ይታወሳል።
አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላምን በሚያደፈርሱ ጽንፈኛ የሕወሃት አመራሮች ላይ የቪዛ እገዳ ጣለች
Jun 18, 2026 256
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላምን ለማደፍረስ እና ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሱ በሚገኙ የቀድሞ የህወሓት ጽንፈኛ አመራሮች እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን አስታወቀች። የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ማዕቀቡ የተጣለው በኢሚግሬሽንና ዜግነት ሕግ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የቪዛ እገዳ በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን በሚያደናቅፉ፣ ሰላምን በሚያናጉ የሕወሃት ጽንፈኛ አባላትና የቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ ያነጣጠረ ነው። አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር ከሚፈልገው የትግራይ ክልል ሕዝብን ጨምሮ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን እንደምትቆም አስታውቃለች። በቀጣናው ሰላምና መረጋጋትን አደጋ ላይ የሚጥሉ የሕወሃት ባለሥልጣናትንና ሌሎች ግለሰቦችን ድርጊት ለማጋለጥ እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማስፈን ዋሽንግተን ያሏትን ዲፕሎማሲያዊ አማራጮች በሙሉ መጠቀሟን እንደምትገፋበትም ገልጻለች።
ስትራቴጂካዊ አጋርነት እና ጂኦ-ፖለቲካዊ ስኬት-የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ጉዞ
Jun 18, 2026 266
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረክ ላይ ያላት ስም፣ዝና እና ተፅዕኖ በአጋጣሚ የተገኘ ሳይሆን፣ዘመናትን በተሻገረ ነፃነት፣በጽኑ ሉዓላዊነትና በብሔራዊ ክብር ላይ የተገነባ የረጅም ዘመን ታሪክ ውጤት ነው። በታሪኳ ያጋጠሟትን የቅኝ ግዛት ወረራ ሙከራዎች በጀግንነትና በዲፕሎማሲያዊ ጥበብ በመመከት፣የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የነፃነት፣የኩራትና የሉዓላዊነት ተምሳሌት ሆና መውጣት ችላለች። ይህ በአድዋ ድል የተመሰከረው ታሪካዊ እውነታ፣ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ድምፅ ለሌላቸው ወገኖቿ በነፃነት እንድትሟገትና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ዋና ተዋናይ እንድትሆን የሞራል ልዕልናን አጎናጽፏታል። የዓለም መንግሥታት ማኅበርና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ግንባር ቀደም መሥራች በመሆን ዓለም አቀፍ ተቋማት ምስረታ ላይ ታሪክ የማይረሳው አሻራ አላት።በአህጉራዊ ድርጅቱ ምስረታና ማዕከልነት ላይ ያላት ተሳርትፎም የዚሁ ማሳያ ነው። ዛሬ ላይ በቀጣናዊ ሰላም ማስከበር፣ በናይል ተፋሰስ የፍትሐዊ ውሃ አጠቃቀም ድርድሮችና እንደ ብሪክስ (BRICS) ባሉ አዳዲስ ዓለም አቀፍ የጂኦ-ፖለቲካ ጥምረቶች ውስጥ ስኬታማ ሆና መቀጠሏን ያመላክታል። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር አላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል።ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ የሚያሳዩ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ከፍታ ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ባደረጓቸው ጥረቶችም የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ፣ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን፣ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ፣የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ኢብራሒም ፣የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳቅ ሄርዞግ፣ የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ዋድፑል እና ሌሎችም ታላላቅ መሪዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች የአዲስ አበባ ቤተኛ አድርጓቸዋል። መሪዎቹ ኢትዮጵያን የሰላም፣የብልጽግና እና የኢኖቬሽን አጋር ናት ሲሉም ይገልጿታል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶችም ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉ አይደሉም። ኢትዮጵያ በቀጣናው እና ዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነት የሚያሳዩ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በኦፊሴላዊ ጉብኝታቸውም ሆነ ወደ ኢትዮጵያ ከሚመጡ የሃገራት መሪዎችና ዲፕሎማቶች ጋር ያደረጓቸው ውይይቶች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ላይ ያተኮሩ የጋራ ተጠቃሚነትንም መነሻ ያደረጉ ናቸው። በአጠቃላይ፣የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ በችግሮችና በትግሎች ውስጥ አልፎ የሀገርን ሕልውና ያቆየ፣ቀጣናዊ ግንኙነትን የፈጠረና አህጉራዊ ትስስርን ያረጋገጠ ታላቅ ጉዞ ነው። በለውጡ ዓመታት በተጠናከረ መልኩ በቀጠለውና ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅምና ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገሩም ናቸው። ሀገሪቱ ያጋጠሟትን ዘመኑ የፈጠራቸውን ውስብስብ የውጭ ጫናዎች በብልሃት በመመከት፣ እንደ ብሪክስ (BRICS) ያሉ ዓለም አቀፍ ጥምረቶች ሙሉ አባል መሆን መቻሏና የሕዳሴው ግድብ የውሃ ዲፕሎማሲን በድል ማጠናቀቋ የለውጥ ዓመታቱ ደማቅ አሻራዎች ናቸው። እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያ በተለዋዋጭ የዓለም ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ስትራቴጂካዊ ተፈላጊነት ከማሳደጋቸውም በላይ፣የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና ቀጣናዊ ተሰሚነት በአስተማማኝ መሠረት ላይ አስቀምጠዋል።
የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የሀገሪቷን ዓለም አቀፍ ተሰሚነትና ስትራቴጂካዊ ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ከፍታ ማደጉን የሚያረጋግጥ ነው
Jun 18, 2026 369
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷና በዓለም አቀፍ መድረኮች የምታሳየው ንቁ ተሳትፎ፣ የሀገሪቷን ዓለም አቀፍ ተሰሚነትና ስትራቴጂካዊ ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ከፍታ ማደጉን የሚያረጋግጥ ነው ሲሉ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ምሁራን ገለጹ። ምሁራኑ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት ባደረገችው እንቅስቃሴ በውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መስክ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ዘላቂ ለማድረግ የበለጠ መሥራት ይገባታል። በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ ባይሳ ተስፋዬ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ ከተማ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማትን በሚመጥን መልኩ መቀየሯ ለዲፕሎማሲው ግንኙነት ትልቅ አቅም ፈጥሯል፡፡   በአዲስ አበባ የተከናወኑት የከተማ ልማት፣ ማስዋብ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ከተማዋን የዓለም የዲፕሎማሲ መስህብ ማድረጉን አመልክተው፤ ይህም የከተማዋን ተወዳዳሪነት ከማሳደጉም በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት በኢትዮጵያ ላይ ያላቸውን እምነት በማሳደግ ሌሎች ድርጅቶችም ወደ ሀገሪቷ ለመምጣት እንዲወስኑ መንገድ መክፈቱንም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች በመምጣት የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን የማደስና የማጠናከር ተግባር ማከናወናቸውን ጠቅሰው፤ የዚህ ዓይነቱ እንቅስቃሴ የኢትዮጵያን ተሰሚነትና ተፅዕኖ ፈጣሪነት እየጨመረ መምጣቱን እንደሚያረጋግጥ ገልጸዋል። በተጨማሪም የአገራት መሪዎች ጉብኝት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጠናከርና ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላቸው የሚያሳይ መሆኑን አስረድተዋል።   ኢትዮጵያ የጣሊያን-አፍሪካ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስርዓተ-ምግብ ጉባኤዎችን በስኬት ማስተናገዷን አስታውሰው፤ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፈረንሶችን በብቃትና በጥራት በማስተናገድ መልካም ስም ማግኘቷ የዓለምን ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ መሳብ እንዳስቻላት ነው የተናገሩት። እነዚህ ስኬቶች የመጡት በሀገር ደረጃ በተከናወኑ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎችና ውጤታማ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የትብብር መድረኮች ያላት ተሳትፎ በየጊዜው እያደገ መምጣቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የሁለትዮሽና የብዝሃ ግንኙነትን በማጠናከርና አዳዲስ ወዳጆችን በማፍራት በኩል በሳል የዲፕሎማሲ ግንኙነት መደረጉን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል ለመሆን መቻሏን በአብነት ገልጸዋል። በተጨማሪም የዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባል ለመሆን እየተከናወነ ያለው ሥራ ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ውስጣዊ ፍላጎቷን እንድታስከብርና ድርሻዋን እንድትወጣ ያግዛታልም ብለዋል።   በአገር ውስጥ የሚሰሩ የአቅም ግንባታ ሥራዎችም ለዓለም አቀፍ ተሰሚነቱ መነሻ መሆናቸውን በመጥቀስ፣ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ለዚህ ማረጋገጫ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያን ቀጣናዊ የመሪነት ሚና ለማስቀጠል፣ የውስጥ አቅምን መገንባት፣ በአንድነት መቆም እና ሁለንተናዊ ልማትን ለማፋጠን መሥራት ይገባል ብለዋል፡፡ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል የውጭ ግንኙነት ፖሊሲና ዲፕሎማሲ መምህር አበራ ሄቢሶ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከለውጡ ወዲህ በፍጥነት እያደገ ያለ የዲፕሎማሲ ሥራ ማከናወን መቻሏን ገልጸዋል። በተለይም በተያዘው ዓመት የጣሊያን፣ ሕንድ፣ ቱርክና ፈረንሳይን ጨምሮ የተለያዩ የዓለም ሀገራት መሪዎች በኢትዮጵያ ይፋዊ ጉብኝት ማድረጋቸው የሀገሪቷን ተሰሚነት ከፍ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ይህም ሀገራቱ ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ መሥራት የጋራ ተጠቃሚነትን እንደሚያረጋግጥ በመገንዘባቸው የመጣ ስኬት መሆኑን አስረድተዋል።   ኢትዮጵያ በመርህ ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ እንደምትከተል ጠቅሰው፤ የብሪክስ አባልነቷም በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላትን የመደራደር አቅም በእጅጉ እንደሚያጎለብተው አስገንዝበዋል። በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የከተማዋን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት የሚመጥኑና የሀገሪቱን ገጽታ ከፍ ያደረጉ መሆናቸውን ያብራሩት መምህር አበራ፤ ኅብረተሰቡ ወደ ሀገር ውስጥ የሚመጡ እንግዶችን በኢትዮጵያዊነት የቆየ የእንግዳ ተቀባይነት ባህል ማስተናገዱን አጠናክሮ ሊቀጥልበት እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ለሚያካሂደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናክሮ ቀጥሏል
Jun 18, 2026 533
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ለሚያካሂደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ለዚህም በዛሬው ዕለት ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪዎች ያዘጋጀውን የግንዛቤና የክህሎት ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።   በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ የአመካካሪዎች ሥልጠና ከዛሬ ሰኔ 11 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ ተጠቁሟል። በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እንደገለጹት፤ ይህ የሥልጠና መርሃ ግብር ልዩነቶች በምክክር የሚፈቱበት፣ በግልጽነትና በመግባባት የሚቀረፉባት ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ በሚደረገው ጉዞ ላይ ሌላ አንድ ትልቅ ምዕራፍና ስኬት ነው። አመካካሪዎች ይህን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በታማኝነት የሚሸከሙ ባለአደራዎች መሆናቸውን የጠቀሱት ፕሮፌሰሩ፤ ራሳቸውን የሀገሪቱን ማኅበራዊ፣ ሕዝባዊና ዴሞክራሲያዊ መጻኢ ዕድል በጋራ የሚገነቡ ታሪክ ሠሪዎች አድርገው ማየት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።   ይህ ሥልጠና አመካካሪዎች የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ክብር የሚጠብቁ እንዲሁም ለሰላም፣ ለፍትሕና ለአንድነት ያላቸውን የጋራ ምኞት የሚያሳኩ ምክክሮችን መምራት የሚያስችላቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና እሴት ለመጨበጥ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ አመካካሪዎች በጉባኤው ወቅት ሁሉም ተሳታፊዎች እኩል የመናገርና የመሳተፍ ዕድል እንዳላቸው ማረጋገጥ፣ በውይይት ወቅት የሚነሱ አለመግባባቶችን በአግባቡ መምራት እንዲሁም ውይይቱ ወደ ጋራ መግባባት እንዲያመራ መንገድ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ አመካካሪዎች ይህንን ትልቅ ሀገራዊ አደራ በትሕትና፣ በገለልተኝነት እና በትዕግሥት እንዲወጡትም አደራ ብለዋል።   በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ዶ በበኩላቸው አመካካሪዎች በሒደት ውስጥ የሚነሱ ልዩ ልዩ ስሜቶችን በአግባቡ መረዳትና መለየት መቻል ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ስሜቶችን በጥንቃቄ በማስተናገድም ወደ ገንቢ የጋራ ተሳትፎ እንዲቀየሩ መርዳት የአመካካሪዎች ዋነኛ ሚና ሊሆን እንደሚገባም ነው አፅንኦት የሰጡት። በኢትዮጵያ የስዊድን ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ ሄድቪግ ሎህም ለምክክሩ ስኬታማነት ስዊድን የበኩሏን እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል።   የሒደቱ አካል የሆኑት አመካካሪዎች በጉባኤው ወቅት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን በቁርጠኝነት መውጣት አለባቸው ብለዋል።
ፖለቲካ
የአሜሪካ የቪዛ ዕገዳ በሰሜን ኢትዮጵያ ለተፈጠረው ውጥረት የጽንፈኛው የህወሃት ቡድንን ተጠያቂ ያደረገ ነው
Jun 18, 2026 320
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የተጣለው የአሜሪካ የቪዛ እገዳ በሰሜን ኢትዮጵያ ላለው ውጥረት መባባስ ቀጥተኛ ተጠያቂ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው ሲሉ የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። አቶ ጌታቸው ረዳ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሰጡት ማብራሪያ እገዳው ከዚህ የጥፋት ቡድን ጋር በጥቅምም ሆነ በስትራቴጂ ይተባበራሉ ተብለው ለሚጠረጠሩ እንደ ሻቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት ላሉ የውጭ አካላትም የተላለፈ ግልጽ ማስጠንቀቂያ ነው። የእርምጃው ትልቅነት በቪዛ መከልከሉ ላይ አይደለም፤ ይልቁንም ዋሽንግተን በኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጠረው አዲስ ውጥረት ተጠያቂነቱን ሙሉ በሙሉ በደብረጽዮን ገብረሚካኤል በሚመራው ቡድን ላይ ማድረጉ ነው ሲሉ ተናግረዋል። አቶ ጌታቸው ይህንኑ እርምጃ ሲያብራሩ የቪዛ እገዳው በተለይ ከደብረጽዮን ጋር በቅርብ የሚሰሩ እና በትግራይ ክልል ለሚታየው ቀውስ መባባስ ምክንያት የሆኑ የሕወሃት አክራሪ አባላትን ለይቶ ያነጣጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላምን ለማደፍረስ እና ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሱ በሚገኙ የቀድሞ የህወሓት ጽንፈኛ አመራሮች እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን አስታውቃለች። የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ማዕቀቡ የተጣለው በኢሚግሬሽንና ዜግነት ሕግ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ የቪዛ እገዳ በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን በሚያደናቅፉ፣ ሰላምን በሚያናጉ የሕወሃት ጽንፈኛ አባላትና የቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ ያነጣጠረ ነው። አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይ ክልል ሕዝብን ጨምሮ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን እንደምትቆም አስታውቃለች። በቀጣናው ሰላምና መረጋጋትን አደጋ ላይ የሚጥሉ የሕወሃት ባለሥልጣናትንና ሌሎች ግለሰቦችን ድርጊት ለማጋለጥ እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማስፈን ዋሽንግተን ያሏትን ዲፕሎማሲያዊ አማራጮች በሙሉ መጠቀሟን እንደምትገፋበትም ገልጻለች።
የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከባንዳና ከባዕዳን ኃይሎች ጋር በመቀናጀት ግጭት ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ይገኛል
Jun 18, 2026 281
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከፈጸመው ግፍ ተጠያቂነት ለማምለጥ ከውስጥና ከውጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በመሻረክ ግጭት ለመፍጠርና በሁከት ለመኖር መወሰኑን በተግባር እያሳየ መሆኑን የስምረት ፓርቲ የምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ምክትል ኃላፊ ጠዓመ ዓረዶም ገለጹ። የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ጠዓመ ዓረዶም በትግራይ ክልል ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊ በሆነበት ወቅት በክልሉ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የፈጠረ መሆኑን ገልጸው፤ በስምምነቱ መሠረት የፌዴራል መንግሥት ተቋርጠው የቆዩትን የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በአፋጣኝ ወደ ሥራ እንዲመለሱ ማድረጉን አንስተዋል። በጦርነቱ ተሳታፊ የነበሩ ወጣቶችን በመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም አማካኝነት ወደ ቀድሞ ኑሯቸውና ሥራቸው እንዲመለሱ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በፌዴራል መንግሥቱ የበጀት ድጋፍም ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው የቀድሞው የሕወሃት ቡድን በህገ ወጥና እኩይ ተግባራት ላይ መሰማራቱን አንስተው፥የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለዳግም ጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል ብለዋል። በዚህም በስምምነቱ መሠረት የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስና ፕሬዚዳንቱን በኃይል ከሥልጣን በማውረድ፣ በህገ ወጥ ምርጫ የተሰየመውን የቀድሞውን ምክር ቤት ወደ ስራ በመመለስ አዲስ ካቢኔ ማዋቀሩን ጠቁመዋል። ቡድኑ ከፌዴራል መንግሥት የሚመደበውን የልማት በጀት ራሱን ለዕኩይ ተግባር መልሶ ለማደራጀት እየተጠቀመበት እንደሚገኝ ነው አቶ ጣዕመ የገለጹት። ይህንን የቡድኑን ሕገ-ወጥ አካሄድ የሚቃወሙ የትግራይ ነዋሪዎችን በማሰርና በማንገላታት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከተጠያቂነት ለማምለጥ ሲል ከውስጥና ከውጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር፣ ክልሉን በሁከትና ብጥብጥ ውስጥ ለማቆየት መወሰኑን በተግባር እያሳየ መሆኑን አስታውቀዋል። የቀድሞ ህወሃት በክልሉ ዳግም የጦርነት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ፓርቲያቸው ባደረገው ዳሰሳ ማረጋገጡን የገለጹት አቶ ጠዓመ፣በርካታ ወጣቶች ያለ ፍላጎታቸው በሌሊት እየታፈሱ ወደ ጦር ካምፕ እየተወሰዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተጨማሪም ቡድኑ ወጣቶችን ለወታደራዊ ሥልጠና ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በአስገዳጅ ሁኔታ በመላክና ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመስራት፣ ሊቀሰቅስ ያሰበውን ጦርነት ቀጣናዊ መልክ ለማስያዝ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የቀድሞው የህወሃት ቡድን ከሀገር ውስጥ ተስፋ ከቆረጡና ከውጭ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ከሚቃወሙ አካላት ጋር "ፅምዶ" የተሰኘ ጸረ ሰላም ጥምረት በመፍጠር ሀገር ለማተራመስ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብና በቀይ ባሕር ጥያቄ ዙሪያ ያገኘችውን ዲፕሎማሲያዊ ተቀባይነት ለማጠልሸት ቡድኑ ከውስጥ ባንዳና ከውጭ ባዕድ ኃይሎች ጋር በቅንጅት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
አሜሪካ በቀድሞው የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች ላይ የወሰደችው እርምጃ የቡድኑን አፍራሽ አካሄድ ለዓለም ያጋለጠ ነው
Jun 18, 2026 295
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- አሜሪካ በቀድሞው የሕወሓት ጽንፈኛ የቡድኑ አመራሮች እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የጣለችው የቪዛ እገዳ፣ የቡድኑን ጽንፈኝነትና አፍራሽ አካሄድ ለዓለም ማኅበረሰብ ያጋለጠ ነው ሲሉ የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ጠዓመ ዓረዶም ገለጹ። አሜሪካ በቀድሞው የሕወሓት ጽንፈኛ አመራሮች እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን መግለጿ ይታወቃል፡፡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ እንደገለጸው፤ የቪዛ እገዳ የተጣለው የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ ተሳታፊ ናቸው በተባሉ አክራሪ የህወሓት አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ ነው፡፡ የስምረት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ጠዓመ ዓረዶም ውሳኔውን አስመልክተው ለኢዜአ እንደገለጹት፣ እርምጃው የአሜሪካ መንግስት የቀድሞው ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን በትግራይ ክልል ውስጥ እያደረገ ያለውን የጦርነት ትንኮሳና የሰላም ስምምነቱን የማፍረስ ሴራ በተገቢው መንገድ የተረዳ መሆኑን የሚያሳይ ነው። አሜሪካ የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ በቅርበት ስትከታተል እንደነበረችም ውሳኔው ማረጋገጫ ነው ሲሉ አክለዋል። ጽንፈኛው ቡድን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ በማፍረስ ጊዜው ያለፈበትንና የፈረሰውን ምክር ቤት በድጋሚ በማዋቀር የራሱን ፕሬዝዳንትና አዲስ ካቢኔ መምረጡ ለግጭትና ሁከት መዘጋጀቱን ያሳያል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ጽንፈኛ ቡድኑ ሰፊ ወታደራዊ ዝግጅትና የጦርነት ትንኮሳዎችን እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ ስለሆነም አሜሪካ በዚህ ወቅት የወሰደችው እርምጃ ለሰላም ፈላጊዎች ትልቅ የምስራች መሆኑን ጠቁመው፤በትግራይ ህዝብ ላይ የሰላም እጦትና ጦርነት የሚደግሰውን ቡድን ለይቶ የመታ ነው ብለዋል። አሁን የተወሰደው እርምጃ የሁሉም የትግራይ ሰላምና የለውጥ ፈላጊ ኃይሎችና የፓርቲያቸው ትግል ያመጣው ውጤት መሆኑን ጠቅሰው፣ሆኖም ግን እርምጃው ከዚህ በላይ ሊጠነክር እንደሚገባ አመልክተዋል። ቡድኑ እስካሁን እያደረገ ያለው ተግባር ግልጽ የአሸባሪነት ስራ ነው ያሉት አቶ ጠዓመ፤ ልክ እንደ ሌሎች ዓለም አቀፍ አሸባሪዎች ሁሉ ይህ ቡድንም በአሜሪካ መንግስትና በዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ዘንድ በልዩ ሁኔታ በአሸባሪነት ሊፈረጅ ይገባል ብለዋል፡፡ የቡድኑን አጥፊ እንቅስቃሴ የዓለም ማኅበረሰብ በሚገባ እንዲገነዘበው ፓርቲያቸው ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የፌዴራል መንግስትም ሕገ-መንግስታዊ ኃላፊነቱን በመጠቀም የቀድሞው ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን ላይ ሕግ የማስከበር ስራውን እንዲወጣ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በምክክር ሂደቱ የታየውን ጠንካራ ትብብርና ተሳትፎ በማስቀጠል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት መቋጨት ይገባል
Jun 18, 2026 231
ሀዋሳ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- በምክክር ሂደቱ የታየውን ጠንካራ ትብብርና ተሳትፎ በማስቀጠል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት መቋጨት እንደሚገባ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፣ ከቀናት በፊት በሰጡት መግለጫ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ላለፉት አራት አመታት አካታች፣ አሳታፊና ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ መዝለቁን አስታውሰዋል፡፡ ከዚህ በመቀጠል ዋናውን የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ገልጸው በዚሁ መሰረት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚካሄድ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የምክክር ሂደቱ ቀጥሎ ዋናው የምክክር ጉባኤ በስኬት እንዲቋጭ የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎ፣ ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን በምክክር ሂደቱ እስካሁን የታየውን የስኬት ጉዞ በማስቀጠል ፍፃሜውን ለሚፈለገው ውጤት ለማብቃት የሁላችንም ትጋት ያስፈልጋል ብለዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ የሥነጽሁፍ መምህር አምሳሌ ሀጥዬ፤ በምክክር ሂደቱ የኮሚሽኑ ብርቱ ጥረትና አጠቃላይ የህዝቡ ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። ምክክሩ የቆዩ ችግሮችን በመፍታት ህብረ ብሄራዊ ሀገራዊ አንድነትን ለማጽናትና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ቁልፍ አበርክቶ የሚኖረው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የታየውን ጠንካራ ትብብርና ተሳትፎ በማስቀጠል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት መቋጨት ይገባል ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የህግና ገቨርናንስ ኮሌጅ መምህር ብሩክ ደስታ፤ የምክክር ሂደቱ ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ በታሪክ አጋጣሚ የተፈጠረ መልካም እድል መሆኑን ገልጸዋል። የእስካሁኑ ሂደት በብዙ መልኩ ዜጎች የተሳተፉበትና የአጀንዳ ማሰባሰቡም ከሁሉም አቅጣጫዎች አካታች በሆነ መልኩ የተካሄደ መሆኑን ተገንዝበናል ብለዋል። በታሪክ አጋጣሚ የተገኘውን ይህንን መልካም እድል በአግባቡ በመጠቀም ለሀገራዊ ችግሮች በምክክር መፈትሄ አበጅቶ መቋጨት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የታየውን የዜጎች ጠንካራ ትብብርና ተሳትፎ በማስቀጠል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ማጠናቀቅ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በዩኒቨርስቲው የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር)፤ በምክክሩ የእስካሁኑ ሂደት የሁሉም ትብብርና ተሳትፎ በጉልህ የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በመጨረሻ የሚፈለገው ውጤት እንዲመጣ መትጋት ለስኬታማነቱም መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መግለጹ ይታወሳል።
አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላምን በሚያደፈርሱ ጽንፈኛ የሕወሃት አመራሮች ላይ የቪዛ እገዳ ጣለች
Jun 18, 2026 256
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላምን ለማደፍረስ እና ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሱ በሚገኙ የቀድሞ የህወሓት ጽንፈኛ አመራሮች እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን አስታወቀች። የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ማዕቀቡ የተጣለው በኢሚግሬሽንና ዜግነት ሕግ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የቪዛ እገዳ በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን በሚያደናቅፉ፣ ሰላምን በሚያናጉ የሕወሃት ጽንፈኛ አባላትና የቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ ያነጣጠረ ነው። አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር ከሚፈልገው የትግራይ ክልል ሕዝብን ጨምሮ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን እንደምትቆም አስታውቃለች። በቀጣናው ሰላምና መረጋጋትን አደጋ ላይ የሚጥሉ የሕወሃት ባለሥልጣናትንና ሌሎች ግለሰቦችን ድርጊት ለማጋለጥ እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማስፈን ዋሽንግተን ያሏትን ዲፕሎማሲያዊ አማራጮች በሙሉ መጠቀሟን እንደምትገፋበትም ገልጻለች።
ስትራቴጂካዊ አጋርነት እና ጂኦ-ፖለቲካዊ ስኬት-የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ጉዞ
Jun 18, 2026 266
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረክ ላይ ያላት ስም፣ዝና እና ተፅዕኖ በአጋጣሚ የተገኘ ሳይሆን፣ዘመናትን በተሻገረ ነፃነት፣በጽኑ ሉዓላዊነትና በብሔራዊ ክብር ላይ የተገነባ የረጅም ዘመን ታሪክ ውጤት ነው። በታሪኳ ያጋጠሟትን የቅኝ ግዛት ወረራ ሙከራዎች በጀግንነትና በዲፕሎማሲያዊ ጥበብ በመመከት፣የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የነፃነት፣የኩራትና የሉዓላዊነት ተምሳሌት ሆና መውጣት ችላለች። ይህ በአድዋ ድል የተመሰከረው ታሪካዊ እውነታ፣ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ድምፅ ለሌላቸው ወገኖቿ በነፃነት እንድትሟገትና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ዋና ተዋናይ እንድትሆን የሞራል ልዕልናን አጎናጽፏታል። የዓለም መንግሥታት ማኅበርና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ግንባር ቀደም መሥራች በመሆን ዓለም አቀፍ ተቋማት ምስረታ ላይ ታሪክ የማይረሳው አሻራ አላት።በአህጉራዊ ድርጅቱ ምስረታና ማዕከልነት ላይ ያላት ተሳርትፎም የዚሁ ማሳያ ነው። ዛሬ ላይ በቀጣናዊ ሰላም ማስከበር፣ በናይል ተፋሰስ የፍትሐዊ ውሃ አጠቃቀም ድርድሮችና እንደ ብሪክስ (BRICS) ባሉ አዳዲስ ዓለም አቀፍ የጂኦ-ፖለቲካ ጥምረቶች ውስጥ ስኬታማ ሆና መቀጠሏን ያመላክታል። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር አላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል።ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ የሚያሳዩ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ከፍታ ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ባደረጓቸው ጥረቶችም የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ፣ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን፣ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ፣የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ኢብራሒም ፣የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳቅ ሄርዞግ፣ የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ዋድፑል እና ሌሎችም ታላላቅ መሪዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች የአዲስ አበባ ቤተኛ አድርጓቸዋል። መሪዎቹ ኢትዮጵያን የሰላም፣የብልጽግና እና የኢኖቬሽን አጋር ናት ሲሉም ይገልጿታል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶችም ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉ አይደሉም። ኢትዮጵያ በቀጣናው እና ዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነት የሚያሳዩ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በኦፊሴላዊ ጉብኝታቸውም ሆነ ወደ ኢትዮጵያ ከሚመጡ የሃገራት መሪዎችና ዲፕሎማቶች ጋር ያደረጓቸው ውይይቶች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ላይ ያተኮሩ የጋራ ተጠቃሚነትንም መነሻ ያደረጉ ናቸው። በአጠቃላይ፣የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ በችግሮችና በትግሎች ውስጥ አልፎ የሀገርን ሕልውና ያቆየ፣ቀጣናዊ ግንኙነትን የፈጠረና አህጉራዊ ትስስርን ያረጋገጠ ታላቅ ጉዞ ነው። በለውጡ ዓመታት በተጠናከረ መልኩ በቀጠለውና ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅምና ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገሩም ናቸው። ሀገሪቱ ያጋጠሟትን ዘመኑ የፈጠራቸውን ውስብስብ የውጭ ጫናዎች በብልሃት በመመከት፣ እንደ ብሪክስ (BRICS) ያሉ ዓለም አቀፍ ጥምረቶች ሙሉ አባል መሆን መቻሏና የሕዳሴው ግድብ የውሃ ዲፕሎማሲን በድል ማጠናቀቋ የለውጥ ዓመታቱ ደማቅ አሻራዎች ናቸው። እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያ በተለዋዋጭ የዓለም ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ስትራቴጂካዊ ተፈላጊነት ከማሳደጋቸውም በላይ፣የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና ቀጣናዊ ተሰሚነት በአስተማማኝ መሠረት ላይ አስቀምጠዋል።
የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የሀገሪቷን ዓለም አቀፍ ተሰሚነትና ስትራቴጂካዊ ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ከፍታ ማደጉን የሚያረጋግጥ ነው
Jun 18, 2026 369
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷና በዓለም አቀፍ መድረኮች የምታሳየው ንቁ ተሳትፎ፣ የሀገሪቷን ዓለም አቀፍ ተሰሚነትና ስትራቴጂካዊ ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ከፍታ ማደጉን የሚያረጋግጥ ነው ሲሉ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ምሁራን ገለጹ። ምሁራኑ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት ባደረገችው እንቅስቃሴ በውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መስክ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ዘላቂ ለማድረግ የበለጠ መሥራት ይገባታል። በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ ባይሳ ተስፋዬ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ ከተማ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማትን በሚመጥን መልኩ መቀየሯ ለዲፕሎማሲው ግንኙነት ትልቅ አቅም ፈጥሯል፡፡   በአዲስ አበባ የተከናወኑት የከተማ ልማት፣ ማስዋብ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ከተማዋን የዓለም የዲፕሎማሲ መስህብ ማድረጉን አመልክተው፤ ይህም የከተማዋን ተወዳዳሪነት ከማሳደጉም በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት በኢትዮጵያ ላይ ያላቸውን እምነት በማሳደግ ሌሎች ድርጅቶችም ወደ ሀገሪቷ ለመምጣት እንዲወስኑ መንገድ መክፈቱንም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች በመምጣት የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን የማደስና የማጠናከር ተግባር ማከናወናቸውን ጠቅሰው፤ የዚህ ዓይነቱ እንቅስቃሴ የኢትዮጵያን ተሰሚነትና ተፅዕኖ ፈጣሪነት እየጨመረ መምጣቱን እንደሚያረጋግጥ ገልጸዋል። በተጨማሪም የአገራት መሪዎች ጉብኝት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጠናከርና ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላቸው የሚያሳይ መሆኑን አስረድተዋል።   ኢትዮጵያ የጣሊያን-አፍሪካ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስርዓተ-ምግብ ጉባኤዎችን በስኬት ማስተናገዷን አስታውሰው፤ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፈረንሶችን በብቃትና በጥራት በማስተናገድ መልካም ስም ማግኘቷ የዓለምን ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ መሳብ እንዳስቻላት ነው የተናገሩት። እነዚህ ስኬቶች የመጡት በሀገር ደረጃ በተከናወኑ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎችና ውጤታማ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የትብብር መድረኮች ያላት ተሳትፎ በየጊዜው እያደገ መምጣቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የሁለትዮሽና የብዝሃ ግንኙነትን በማጠናከርና አዳዲስ ወዳጆችን በማፍራት በኩል በሳል የዲፕሎማሲ ግንኙነት መደረጉን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል ለመሆን መቻሏን በአብነት ገልጸዋል። በተጨማሪም የዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባል ለመሆን እየተከናወነ ያለው ሥራ ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ውስጣዊ ፍላጎቷን እንድታስከብርና ድርሻዋን እንድትወጣ ያግዛታልም ብለዋል።   በአገር ውስጥ የሚሰሩ የአቅም ግንባታ ሥራዎችም ለዓለም አቀፍ ተሰሚነቱ መነሻ መሆናቸውን በመጥቀስ፣ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ለዚህ ማረጋገጫ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያን ቀጣናዊ የመሪነት ሚና ለማስቀጠል፣ የውስጥ አቅምን መገንባት፣ በአንድነት መቆም እና ሁለንተናዊ ልማትን ለማፋጠን መሥራት ይገባል ብለዋል፡፡ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል የውጭ ግንኙነት ፖሊሲና ዲፕሎማሲ መምህር አበራ ሄቢሶ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከለውጡ ወዲህ በፍጥነት እያደገ ያለ የዲፕሎማሲ ሥራ ማከናወን መቻሏን ገልጸዋል። በተለይም በተያዘው ዓመት የጣሊያን፣ ሕንድ፣ ቱርክና ፈረንሳይን ጨምሮ የተለያዩ የዓለም ሀገራት መሪዎች በኢትዮጵያ ይፋዊ ጉብኝት ማድረጋቸው የሀገሪቷን ተሰሚነት ከፍ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ይህም ሀገራቱ ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ መሥራት የጋራ ተጠቃሚነትን እንደሚያረጋግጥ በመገንዘባቸው የመጣ ስኬት መሆኑን አስረድተዋል።   ኢትዮጵያ በመርህ ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ እንደምትከተል ጠቅሰው፤ የብሪክስ አባልነቷም በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላትን የመደራደር አቅም በእጅጉ እንደሚያጎለብተው አስገንዝበዋል። በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የከተማዋን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት የሚመጥኑና የሀገሪቱን ገጽታ ከፍ ያደረጉ መሆናቸውን ያብራሩት መምህር አበራ፤ ኅብረተሰቡ ወደ ሀገር ውስጥ የሚመጡ እንግዶችን በኢትዮጵያዊነት የቆየ የእንግዳ ተቀባይነት ባህል ማስተናገዱን አጠናክሮ ሊቀጥልበት እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ለሚያካሂደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናክሮ ቀጥሏል
Jun 18, 2026 533
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ለሚያካሂደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ለዚህም በዛሬው ዕለት ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪዎች ያዘጋጀውን የግንዛቤና የክህሎት ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።   በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ የአመካካሪዎች ሥልጠና ከዛሬ ሰኔ 11 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ ተጠቁሟል። በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እንደገለጹት፤ ይህ የሥልጠና መርሃ ግብር ልዩነቶች በምክክር የሚፈቱበት፣ በግልጽነትና በመግባባት የሚቀረፉባት ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ በሚደረገው ጉዞ ላይ ሌላ አንድ ትልቅ ምዕራፍና ስኬት ነው። አመካካሪዎች ይህን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በታማኝነት የሚሸከሙ ባለአደራዎች መሆናቸውን የጠቀሱት ፕሮፌሰሩ፤ ራሳቸውን የሀገሪቱን ማኅበራዊ፣ ሕዝባዊና ዴሞክራሲያዊ መጻኢ ዕድል በጋራ የሚገነቡ ታሪክ ሠሪዎች አድርገው ማየት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።   ይህ ሥልጠና አመካካሪዎች የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ክብር የሚጠብቁ እንዲሁም ለሰላም፣ ለፍትሕና ለአንድነት ያላቸውን የጋራ ምኞት የሚያሳኩ ምክክሮችን መምራት የሚያስችላቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና እሴት ለመጨበጥ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ አመካካሪዎች በጉባኤው ወቅት ሁሉም ተሳታፊዎች እኩል የመናገርና የመሳተፍ ዕድል እንዳላቸው ማረጋገጥ፣ በውይይት ወቅት የሚነሱ አለመግባባቶችን በአግባቡ መምራት እንዲሁም ውይይቱ ወደ ጋራ መግባባት እንዲያመራ መንገድ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ አመካካሪዎች ይህንን ትልቅ ሀገራዊ አደራ በትሕትና፣ በገለልተኝነት እና በትዕግሥት እንዲወጡትም አደራ ብለዋል።   በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ዶ በበኩላቸው አመካካሪዎች በሒደት ውስጥ የሚነሱ ልዩ ልዩ ስሜቶችን በአግባቡ መረዳትና መለየት መቻል ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ስሜቶችን በጥንቃቄ በማስተናገድም ወደ ገንቢ የጋራ ተሳትፎ እንዲቀየሩ መርዳት የአመካካሪዎች ዋነኛ ሚና ሊሆን እንደሚገባም ነው አፅንኦት የሰጡት። በኢትዮጵያ የስዊድን ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ ሄድቪግ ሎህም ለምክክሩ ስኬታማነት ስዊድን የበኩሏን እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል።   የሒደቱ አካል የሆኑት አመካካሪዎች በጉባኤው ወቅት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን በቁርጠኝነት መውጣት አለባቸው ብለዋል።
ማህበራዊ
ኢትዮጵያ በርካታ ስደተኞችን በማስተናገድ የአፍሪካውያንን የጋራ መረዳዳት እሴት በተግባር እያሳየች ነው
Jun 18, 2026 224
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ በርካታ ስደተኞችን በማስተናገድ የአፍሪካውያንን የጋራ መረዳዳት እሴት በተግባር እያሳየች መሆኗን የአፍሪካ ሕብረት የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ ገለጹ። የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ስደተኞች በመጠለያ ጣቢያዎች ያላቸውን ሕይወት ከሀገራዊ ሥርዓቶች ጋር ማስተሳሰርን ማዕከል ያደረገ አዲስ የማካተት ፍኖተ-ካርታ ይፋ አድርጓል፡፡   የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ከቀጣናው በሙሉ ለሚመጡ ስደተኞች የምታሳየውን የረጅም ጊዜ የእንግዳ ተቀባይነት ባህልና አጋርነት ሕብረቱ ትልቅ ግምት እንደሚሰጠው ገልጸዋል። ባለፉት በርካታ አሥርት ዓመታት ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞችን ከለላ በመስጠት ለአፍሪካውያን ኩራት የሆነውን የጋራ መረዳዳትና ኃላፊነትን በተግባር ማሳየቷን ጠቁመዋል። አዲሱ የማካተት ፍኖተ-ካርታ በዚህ ኩሩ ታሪካዊ ቅርስ ላይ የተገነባ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በጠንካራ አጋርነት እና ቀጣይነት ባለው የፖለቲካ ቁርጠኝነት የተደገፈ ሀገራዊ አመራር የተገኘ ትልቅ ውጤት መሆኑን አብራርተዋል። ፍኖተ-ካርታው ስደተኞች እና አስተናጋጁ ማኅበረሰብ በጋራ ሊበለጽጉና ሊያድጉ የሚችሉባቸውን አዳዲስ ዕድሎች የሚያሳይ መሆኑንም አክለዋል።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ምክትል ዋና ጸሐፊ መሀመድ አብዲ ዋሬ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ተራማጅና አካታች የሆኑ የስደተኞች ፖሊሲዎችን በማውጣትና በማሳደግ ረገድ ለአፍሪካ በአርአያነት የምትጠቀስ ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። አሁን ይፋ የሆነው የማካተት ፍኖተ-ካርታ የዘመናችንን እጅግ አጣዳፊና ውስብስብ የስደተኞች ፈተናዎች ለመፍታት ኢትዮጵያ ያላትን ግልጽ ራዕይና የማይናወጥ ቁርጠኝነት በአጽንኦት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትርክት ግንባታ ያላትን የመሪነት ሚና አጠናክራ ትቀጥላለች
Jun 18, 2026 215
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትርክት ግንባታ ላይ ያላትን ቀዳሚና የመሪነት ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ በስኬት እንዲካሄድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል፡፡   በዚሁ የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ፣ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ከተለያዩ ተቋማት የተወጣጡ ተወካዮችና የክብር እንግዶች ተገኝተዋል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና በኤ.ጂ.ኤ.ቴክ ኢንተርፕራይዝ ትብብር በአዲስ አበባ ከተማ መካሄዱ ይታወቃል። ሚያዚያ 29 እና ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደው በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ተሳትፈዋል። ተሳታፊዎቹ በአዲስ አበባና በተለያዩ የሀገሪቷ ክልሎች የተከናወኑ ታላላቅ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።   ጉባዔው የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና የዲጂታል ትርክቱን አህጉሪቱ እራሷ በባለቤትነት እንድትመራው ያለመ ሲሆን፤ እቅዱንና ዓላማውን ሙሉ በሙሉ ያሳካ ውጤታማ መድረክ ሆኖ ተጠናቋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የቦርድ ሰብሳቢ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ትርክት መገንባት ለአጠቃላይ የአፍሪካ ትርክት ግንባታ ወሳኝ መሰረት ነው። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ስኬቶች በስፋት መነገር መጀመራቸው አፍሪካ ቀና እንድትል እያደረጋት ከመሆኑም በላይ፤ መሬት ላይ ያለውን እውነታ ለዓለም ማስተዋወቅ ተችሏል ብለዋል። ስለ ኢትዮጵያና አፍሪካ ትክክለኛውን ታሪክና እውነታ ለዓለም ማሳወቅ ብሎም ከዚህ ቀደም የተፈጠሩ አፍራሽ ግንዛቤዎችን ለመቀየር ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን የሚጫወቱትን ሚና ከመቼውም ጊዜ በላይ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡ ፡ ጉባኤው ሊጠናከር የሚገባው በጎ ጅምር መሆኑን በመጥቀስም ለስኬቱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።   የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጉባኤው የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ በገነባ መልኩ እጅግ ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በቅንጅት የተሰራው ስራ ለውጤታማነቱ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመው፤ የቱሪዝም ሚኒስቴር መሰል አህጉራዊ ፋይዳ ያላቸው ታላላቅ ጉባኤዎች በቀጣይም በተጠናከረ መልኩ እንዲካሄዱ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሁሉ እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ በጉባኤው ላይ በድምሩ ከ480 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያላቸው 200 የሀገር ውስጥና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሳተፋቸውን ተናግረዋል፡፡   መድረኩ ኢትዮጵያ በልማት ዘርፍና ለአፍሪካ ገጽታ ግንባታ ምን ያህል ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነች እንደሆነ ማሳየት የተቻለበት መሆኑን ጠቁመው፤ የሀገሪቷን የቱሪዝም ሀብቶች ለማስተዋወቅ የረዳ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ጠቅሰዋል። የኤ ጂ ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር አብዲ ጠና በበኩላቸው፤ ጉባኤው በአፍሪካ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች እርስ በእርስ እንዲተዋወቁና ለጋራ ዓላማ አብረው እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በንግግራቸው አንስተዋል።
ኢንስቲትዩቱ የፋርማሲዩቲካል የምርምር ውጤቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ከመገናኛ ብዙኃን ጋር ያለውን አጋርነት ያጠናክራል 
Jun 18, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ አርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የሚያወጣቸውን አዳዲስ የፋርማሲዩቲካል የምርምር ውጤቶች ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ከመገናኛ ብዙኃን ጋር ያለውን አጋርነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ "ምርምርና ሚዲያ ለላቀ ጤና" በሚል መሪ ሐሳብ አራተኛውን ዓመታዊ የሚዲያ ፎረም አካሂዷል፡፡ በፎረሙ ላይ ከተለያዩ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ተቋማት የተወጣጡ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን፣ በኢንስቲትዩቱ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎችንና የምርምር ውጤቶችን በቦታው ተገኝተው ጎብኝተዋል።   የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ህክምና በዓለም ላይ ኢትዮጵያ ከምትታወቅባቸው የቀደሙ የስልጣኔ ዘርፎች አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የትልልቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት መስራችና የህክምና ጠበብቶች መፍለቂያ መሆኗን አመልክተዋል። የህክምና አሰራሩ ዘመናዊ መንገድን የተከተለ ባለመሆኑ ዘርፉ እንደ እድሜው ያህል ወደፊት መጓዝ ሳይችል መቆየቱን ጠቁመው፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ሀገር በቀል እውቀትን በዘመናዊ አግባብ መምራት በመቻሉ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል። የህክምናውን ዘርፍ በምርምር የተደገፈ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉም ብለዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ የመድኃኒት፣ የክትባትና የመመርመሪያ መሣሪያዎች ምርምርና ልማትን እንዲሁም የፋርማሲዩቲካል ኢንዱስትሪውን በስፋት እየደገፈ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በዚህም ማዕቀፍ የተከናወኑ ተግባራት የሀገር ውስጥ የፋርማሲዩቲካል ኢንዱስትሪው ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እየሆነ እንዲመጣ ማድረጋቸውንና በአሁኑ ወቅት የክትባት መድኃኒቶች በራስ አቅም ተመርተው ለህብረተሰቡ ተደራሽ እየሆኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የኢንስቲትዩቱን የምርምር ውጤቶች ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የሚዲያ ሚና የማይተካ መሆኑን የገለጹት ፕሮፌሰሩ፤ በቀጣይም የሚወጡ አዳዲስ የፋርማሲዩቲካል የምርምር ውጤቶችን ለህዝብ ለማድረስ ከሚዲያ አካላት ጋር ያለው አጋርነት ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በጉብኝቱና በፎረሙ ላይ የተሳተፉት የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በበኩላቸው፤ ኢንስቲትዩቱ የሀገሪቱን የህክምና ዘርፍ ለማዘመን እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት እጅግ የሚደነቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የተቋሙን የሪፎርም እና የምርምር ስራዎች በዘገባዎቻቸው ውስጥ በስፋት በማካተት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰሩ ጠቅሰዋል፡፡
የጤና ነገር
Jun 18, 2026 166
በዮሐንስ ደርበው በወቅቱ ካልታከመ ለኩላሊት መድከም፣ ለደም መመረዝና ለሞት የሚያደርሰው ኢንፌክሽን · የሕጻናት የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን እንዴት ይከሰታል? ምንም እንኳን አልፎአልፎ አንድ ኩላሊት ኖሯቸው የሚወለዱ ሕጻናት ቢኖሩም፤ ጤናማ (ኖርማል) የሚባለው በግራና በቀኝ ሁለት ኩላሊት ኖሮት መወለድ መሆኑን የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። የኩላሊት አንዱ ሥራም ሽንት ማጣራት መሆኑን የሚገልጹት ከፍተኛ የሕጻናት ሐኪም የሆኑት ዶክተር ሎዛ ኑርልኝ፤ በዚህ ሂደት የተመረተው ሽንት ከሰውነት (ወደ ውጭ) ይወገዳል ይላሉ። በግራና በቀኝ ኩላሊት የተጣራው ሽንት ወደ ሽንት ፊኛ እንደሚተላለፍና በሽንት ቱቦ አማካኝነት ከሰውነት (ወደ ውጭ) እንደሚወገድ ያስረዳሉ። ይህ ሂደት (ስትራክቸር) በአግባቡ የሚከናወነው ከባክቴሪያ የጸዳ ሲሆን መሆኑንም ይገልጻሉ። በአንጻሩ ሂደቱ (ኩላሊት፣ የሽንት ፊኛ እና ሽንት የሚወገድበት ቱቦ በባክቴሪያ ሲጠቃ) የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ተከሰተ እንደሚባል ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። · የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን እነማንን ያጠቃል? የሕክምና ባለሙያዋ እንዳሉት፤ የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ሕጻናትን በስፋት ያጠቃል። በሕጻናት ላይ የተለመደ የኢንፌክሽን ዓይነት ስለመሆኑም ገልጸዋል። በተለይም ከአንድ ዓመት በታች የሆኑ ሕጻናት በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ መሆናቸውን ጠቁመው ሁኔታውን በአኃዝ ሲያስረዱ፤ ከ100 ሕጻናት 7ቱ ለሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ተጋላጭ መሆናቸውን አብራርተዋል። በጾታ ደረጃ ወንዶችም ሴቶችም ተጋላጭ መሆናቸውን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ በተለይም ያልተገረዙና ከ3 ወር በታች ዕድሜ ያላቸው ወንድ ሕጻናት በስፋት እንደሚጠቁ ጠቁመው በዚህም ከ100 ሕጻናት 20ዎቹ እንደሚጠቁ የጥናት ውጤቶች ያመላክታሉ ብለዋል። በአንጻሩ ከአንድ ዓመት በላይ በሆናቸው ሕጻናት ላይ ደግሞ በይበልጥ ሴቶች እንደሚጋለጡ ጠቁመዋል። ለዚህም ሴት ከመሆን ጋር ተያያዙ የተለያዩ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች እንዳሉ አንስተዋል። · የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ምልክቶች ምንድን ናቸው? የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ህመሙ (ኢንፌክሽኑ) እንደተከሰተበት ቦታ ምልክቶቹ እንደሚለያዩ አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ኩላሊት ላይ ወይም የሽንት ፊኛ ላይ ወይም የሽንት ማስወገጃ ቱቦ ላይ የሚከሰት ኢንፌክሽን ቢኖር ምልክቱ የተለያየ መሆኑን አስረድተዋል። ይህን በምሳሌ ሲያስረዱም የሽንት ፊኛ ወይም ሽንት የሚወገድበት ቱቦ በኢንፌክሽን ሲጠቃ፤ ቶሎ ቶሎ ሽንት የመሽናት ሁኔታ፣ በሚሸኑበት ወቅት የማቃጠል ስሜት፣ የሽንት ቀለም መደፍረስ፣ አንዳንድ ጊዜ ሽታ ያለው ሽንት መኖር፣ ከእምብርት በታች የህመም ስሜት መኖር የሚሉትን አንስተዋል። ኢንፌክሽኑ ኩላሊት ላይ ሲከሰት ደግሞ ይላሉ፤ በጣም ታምመው ወደ ሕክምና የመሄድ ሁኔታ መኖር (ከፍተኛ ትኩሳት መኖር፣ ማቅለሽለሽ (ማስመለስ)፣ በጎንና በጎን እንዲሁም በጀርባቸው የህመም ስሜት መኖር) የሚሉት ምልክቶች ሊታዩ እንደሚችሉ አብራርተዋል። ከአንድ ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ደግሞ ከላይ የተገለጹት ሁሉም ምልክቶች ላይታዩባቸው እንደሚችሉ በመጠቆም፤ ትኩሳት ብቻ፣ ማስመለስ ብቻ፣ የሆድ ህመም ብቻ ሊከሰትባቸው እንደሚችል አስገንዝበዋል። የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ጨቅላ ሕጻናትንም (ወዲያው በተወለዱበት ቅጽበት) ሊያጠቃ እንደሚችል ገልጸዋል። በዚህ ወቅትም ምልክቶቹ፤ መነጫነጭ፣ ክብደት መቀነስ፣ ጡት መጥባት መቀነስ፣ እንቅስቃሴ መቀነስ፣ ቢጫ መሆን ሊሆን እንደሚችል አስረድተዋል። · ወደ ሕክምና መቼ ይሂዱ? ዶክተር ሎዛ እንደገለጹት፤ በተለይም ከአንድ ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ላይ ሁሉም የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ምልክቶች ላይታዩ እንደሚችሉ ወላጆች (አሳዳጊዎች) መገንዘብ አለባቸው። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ ከሁለት ቀን በላይ የቆየ ከፍተኛ ትኩሳት (የሙቀት መጠኑ ከ39 እስከ 40ና በላይ የሆነ) ሲኖር የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ሊሆን ስለሚችል ወላጆች (አሳዳጊዎች) ሕጻናቱን ቶሎ ወደ ሕክምና እንዲወስዱ አሳስበዋል። ከአንድ ዓመት በላይ በሆኑ ሕጻናት ላይም ከላይ የተገለጹት ምልክቶች ሲስተዋሉ ቶሎ ወደ ሕክምና መውሰድ እንደሚመከር አስገንዝበዋል። · የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽንን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? እንደ ሕክምና ባለሙያዋ ምክር፤ ወላጆች ልጆችን በሚያጸዳዱበት ወቅት ከኋላ ወደ ፊት አለማጽዳት (ከሰገራ መውጫ ወደ ሽንት መሽኛ አቅጣጫ አለማጸዳዳት)፣ ጥብቅ ያለ (እንደ ታይት ያለና መሰል) ልብስ አለማልበስ፣ ሽንት እንዳይቋጥሩ ማድረግ (ሽንታቸው መምጣቱን በመጠየቅ ወይም ሲመጣባቸው ቶሎ ቶሎ እንዲሸኑ ማበረታታት)፣ ድርቀት ካለባቸው ይህን መከላከል፣ በየ6 ወሩ የትላትል መድኃኒት እንዲወስዱ ማድረግ እና የሕጻናትን ጥፍር ማሳጠር ኢንፌክሽኑን ቀድሞ ለመከላከል የሚያግዙ ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው። · ሕክምናው የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ኬዙ (ኢንፌክሽኑ) እንደተከሰተበት ቦታ እና እንደ ልጆቹ ዕድሜ እንደሚለያይ በማስገንዘብ፤ ከላይ ምልክቶች ብለን ያስቀመትናቸው ሲከሰቱ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድ በቀላሉ ታክመው እንዲድኑ ማድረግ እንደሚቻል ዶክተር ሎዛ አስገንዝበዋል። የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ቶሎ ካልታከመ ከኩላሊት መድከም እስከ ደም ኢንፌክሽን (ደም መመረዝ) ድረስ የከፋ ጉዳት እንደሚያስከትል እና ከዚህም ሲያልፍ እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል ገልጸዋል። #የጤና_ነገር #የሽንት_ቧንቧ_ኢንፌክሽን #ኢዜአ
ኢኮኖሚ
በፌዴራል ዋና ኦዲተር የኦዲት ሽፋን፣ ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች የሚበረታቱ ናቸው 
Jun 18, 2026 176
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- የፌዴራል ዋና ኦዲተር የኦዲት ሽፋንን ጥራትና ተደራሽነት ለማሳደግ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን የሕዝብ ተወካዮች የምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ26ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የፌዴራል ዋና ኦዲተር ያቀረበውን የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የፋይናንሺያል፣ የሕጋዊነት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ላይ ተወያይቷል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ሪፖርቱን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። ዋና ኦዲተሯ በሪፖርታቸው፤ በተቋማት በጀት አጠቃቀም፣ በተሰብሳቢ ሒሳብ መጠን እንዲሁም በፕሮጀክቶች ውል መቋረጥ ላይ መሻሻሎች መታየታቸውን አንስተዋል።   የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ የፌዴራል ዋና ኦዲተር የኦዲት ሽፋን ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ እያከናወናቸው የሚገኙት ሥራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በየዓመቱ የሚቋረጡ ፕሮጀክቶች ቁጥር እያነሰ መምጣቱን ሪፖርቱ የሚያመላክት መሆኑን ያነሱት የምክር ቤት አባላቱ፤ የኦዲት ጥራትንና ግልጽነትን ለማጠናከር በፌዴራል ዋና ኦዲተር በኩል እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችንም አድንቀዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ በበኩላቸው፤ የኦዲት ጥራትን ለማሻሻል በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞም የተቋማትን የውስጥ ኦዲት ጥራት የሚያሻሽሉ የአቅም ግንባታ ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ዋና ኦዲተሯ አስረድተዋል። የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር)፤ በ2017 በጀት ዓመት ለልማት ሥራዎች ከተመደበው በጀት ውስጥ የዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የ99 ነጥብ 3 በመቶ የኦዲት ሽፋን ማሳካት መቻሉን አስታውቀዋል።   በተጨማሪም የክዋኔ ኦዲት ትግበራ በየዓመቱ እያደገ መምጣቱ የተቋሙን የኦዲት አቅም ውጤታማነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ አክለውም፤ በየበጀት ዓመቱ በምክር ቤቱ የሚጸድቀው የኦዲት ሽፋን ሙሉ በሙሉ እንዲካሄድና ለክዋኔ ኦዲትም በቂ ሽፋን እንዲኖር ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ ይገባቸዋል ብለዋል። የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፤ የፌዴራል ዋና ኦዲተር ተወዳዳሪና ጠንካራ አሠራርን ለማጎልበት እያከናወናቸው የሚገኙት ተግባራት የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ምክትል አፈ ጉባኤዋ በየዓመቱ እየተገኙ ያሉ ለውጦችን ይበልጥ በማሳደግ እንዲሁም የታዩ ውስንነቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የቅንጅት ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከጎሮ እስከ ኮዬ ፈጬ አደባባይ ያለው አዲስ የኮሪደር ልማት ስራ ተጀመረ
Jun 18, 2026 184
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከጎሮ እስከ ኮዬ ፈጬ አደባባይ ድረስ ያለውን አዲስ የኮሪደር ልማት ስራ በተቀናጀና በተደራጀ አግባብ መጀመሩን አስታወቁ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመልእክታቸው፤ ከጎሮ መታጠፊያ እስከ ኮዬ ፈጬ አደባባይ ያስጀመርነው የኮሪደር ልማት አጠቃላይ የመንገዱ ርዝመት 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ሲሆን፣ የመንገዱ ስፋት 70 ሜትር (ስምንት ሌን ያለው) ሆኖ ከነግሪነሪው 124 ሜትር ስፋት እንደሚኖረው ገልጸዋል።   ከዚህም በተጨማሪ 21 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የሳይክል መንገድ፣ 21 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና በሁለቱም በኩል 4.5 ሜትር ስፋት ያለው የእግረኛ መንገድ፣ ሰፊ የአረንጓዴ ሽፋን እንዲሁም የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ በውስጡ እንደሚኖረው አመልክተዋል። ይህ የኮሪደር ልማት በከተማዋ ቀደም ሲል የለሙ መሰረተ ልማቶችን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያስተሳስር፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን የሚያነቃቃ እና በመንገዱ ላይ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ የሚፈታ መሆኑን አመልክተዋል። መነሻውን ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር ያደረገ በመሆኑም ሀገራዊ ሁነቶችን ለማስተናገድ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥርና የአካባቢውን ስታንዳርድ በእጅጉ በሚያሳድግ ሁኔታ እንደሚሰራም ነው ያብራሩት።   በኮሪደሩ ላይ ሞሎች፣ የቢዝነስ ተቋማት እና ሌሎች ኮሚኒቲዎች እንደሚገነቡ ገልጸው ከዚህ ቀደም በመንገዱ ዙሪያ ከደረጃ በታች ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን ከፍ ባለ ደረጃ ለመስጠት በሚያስችል መልኩ በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትልቅ ርብርብ እንደሚሰራም ከንቲባዋ ጠቁመዋል። ይህ ኮሪደር ከከተመዋ አልፎ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው፣ ለአካባቢው ነዋሪ ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር፣ አካባቢውን ወደ ትልቅ የንግድ እንቅስቃሴ የሚቀይር ነው ብለዋል። በአካባቢው ላይ የሚኖሩ የከተማዋ ነዋሪዎች ትብብራቸው እንደ ወትሮው የተጠናከረ እንዲሆንና አብረን እንድንሰራ፤ እንዲሁም በስራው ውስጥ የሚሳተፉ ኮንትራክተሮች፣ ማህበራት፣ አማካሪዎች በአጠቃላይ ባለድርሻ አካላት በትብብር በፍጥነት በጋራ እንዲሳካ ከንቲባዋ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለቤቶች ልማት የአገር ውስጥ የፋይናንስ አቅምን በውጤታማነት ለመጠቀም እየሰራ ነው
Jun 18, 2026 172
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለቤቶች ልማት ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ የፋይናንስ አቅምን በውጤታማነት ለመጠቀም እየሰራ እንደሚገኝ የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ ረሻድ ከማል (ዶ/ር) ገለጹ። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና የኦሮሚያ ባንክ የስትራቴጂካዊ አጋርነት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የተፈራረሙት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተፈሪ መኮንን ናቸው።   ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውናቸው የቤት ልማትና ተያያዥ ሥራዎች አስተማማኝ የፋይናንስ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን በማረጋገጥ ረገድ ስምምነቱ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተመላክቷል። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ረሻድ ከማል (ዶ/ር)፤ ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውነው ሰፊ የቤት ልማት ፕሮግራም የአገር ውስጥ የፋይናንስ አቅምን በውጤታማነት ለመጠቀም በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የኦሮሚያ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተፈሪ መኮንን በበኩላቸው፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስሙ በለውጥና በስኬት ከሚነሳው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር መሥራት ለአገር ኢኮኖሚ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል። ሁለቱ ወገኖች ለስምምነቱ ተፈጻሚነት ያላቸውን ከፍተኛ ቁርጠኝነት መግለጻቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።
በምስራቅ ወለጋ ዞን ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በኢንቨስትመንት ዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን እየሰራን ነው-ባለሀብቶች 
Jun 18, 2026 174
ነቀምቴ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ወለጋ ዞን ለኢንቨስትመንት ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ውጤታማ ለመሆን እየሰሩ መሆናቸውን በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ባለሀብቶች ገለጹ። በዞኑ ሊሙ ወረዳ በግብርናው ዘርፍ በበቆሎ ምርት ላይ የተሰማሩት ባለሀብት አቶ አበራ ጎሹ እንደገለጹት፤ በአካባቢው ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የግብርና ምርትና ምርታማነትን እያሳደጉ ይገኛሉ። በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግረው በ8 ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል በ100 ሄክታር መሬት ላይ በቆሎ እያመረቱ መሆኑን ገልጸዋል። የግብርና ሥራውን በማዘመን ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጡ መሆኑንና ይህም ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጥሩ አርዓያ እየሆነ መምጣቱን ጠቁመዋል። በእርሻ ስራውም ለ9 ሰዎች ቋሚ፣ እንዲሁም በምርት ወቅት ከ50 እስከ 60 ለሚደርሱ ነዋሪዎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አስረድተዋል። ሌላኛው ባለሀብት አቶ ረጋሳ ኤጄታ በበኩላቸው፣ በሲቡ ስሬ ወረዳ ለሊሳ ቀበሌ በግብርና ሥራ ላይ መሰማራታቸውን ገልጸዋል። መንግስት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ዜጎች በተሰማሩበት ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ እያደረገ ያለውን ድጋፍና ምቹ ሁኔታ በመጠቀም እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ባለሀብቱ በቆሎ፣ ሩዝ፣ ኑግ እና አኩሪ አተር የተሻለ ምርት የሚገኝባቸው ሰብሎች መሆናቸውን ገልጸው በምርት ወቅት ከ100 እስከ 150 ለሚደርሱ የአካባቢው ነዋሪዎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።   የምስራቅ ወለጋ ዞን ኢንቨስትመንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ተስፋ፤ በዞኑ ሰፊ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ መኖሩን ገልጸው፤ ባለሀብቶች በተለይም በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን እና በግብርና ዘርፎች ላይ በስፋት መሰማራታቸውን ተናግረዋል። በዞኑ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች 1 ሺህ 392 ባለሀብቶች በሥራ ላይ መሆናቸውን ገልጸው እነዚህ ባለሀብቶች በ2 ቢሊዮን ብር ካፒታል እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል። በዞኑ በተመቻቸው የኢንቨስትመንት ዕድል 66 ሺህ ሄክታር መሬት ለባለሀብቶች የተሰጠ ሲሆን እስካሁን ከ26 ሺህ በላይ ወጣቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ተናግረዋል። ዞኑ በተለይ ለግብርና ሥራዎች ተመራጭ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፤ በቆሎ፣ የቅባት እህሎች፣ የጥራጥሬ ሰብሎች፣ ቡና እና ሌሎች የአገዳ እህሎች በስፋት የሚመረቱበት አካባቢ መሆኑን ገልጸዋል። በመሰረተ ልማት አቅርቦት ረገድ ያሉ ጥያቄዎችንም ደረጃ በደረጃ ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ ከ312 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችል የፀሀይ ኃይል ማመንጫ ሊገነባ ነው
Jun 18, 2026 236
ሀዋሳ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ ከ312 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችል የፀሀይ ኃይል ማመንጫ ሊገነባ ነው። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሡልጣን ወሊ (ዶ/ር) የግንባታ ፕሮጀክቱን ያስጀመሩ ሲሆን ግንባታው ሲጠናቀቅ ለመስኖ ልማት ስራ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጥረት በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።   ለዚህም የመስኖ ልማትን ይበልጥ የማስፋፋትና ያልታረሱ መሬቶችን ማልማት አስፈላጊ መሆኑን አንስተው ለልማቱ ስኬት የሃይል ልማትን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። በግብርና ልማቱ በነዳጅ ኃይል የሚሰሩ የመስኖ ፕሮጀክቶች መስተጓጎል እንዳይገጥማቸው የጸሃይና ሌሎች የሃይል አማራጮችን መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። በዚሁ መሰረትም በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ በአሳራዶ ሜሮ ቀበሌ የሚገነባው የፀሀይ ኃይል ማመንጫ ከ312 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የፕሮጀክቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ ከ312 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ከማልማት በተጨማሪ ከ800 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው አርሶ አደሮች ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል። የሲዳማ ክልል ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ከበደ ጋኖሌ፤ የፕሮጀክቱ ግንባታ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት መስመር ለራቁ ገጠራማ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ እንዲሁም ለመስኖ ልማት የሃይል ምንጭ ሆኖ ያገለግላል ብለዋል።   አካባቢው የአቮካዶና መሰል የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የቡና ልማት ሰፊ አማራጭ ያለበት በመሆኑ የፕሮጀክቱ ግንባታ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑንም አንስተዋል። የከርሰና ገጸ ምድር የውሃ አማራጭን በመጠቀም የእርሻ ስራን የማጠናከር ስራ በስፋት መቀጠሉን ጠቅሰው ባለፉት አምስት ዓመታት ከ60 በላይ የመስኖ ፕሮጀክቶች መገንባታቸውንም አስታውሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በምርምርና በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት የጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር ያጠናክራል
Jun 18, 2026 230
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በምርምር ሥራዎችና በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ። በዩኒቨርሲቲው በምርምር ፕሮጀክቶች እና በማህበረሰብ አገልግሎቶች የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምግምና ቅንጅታዊ ሥራን ለማጠናከር ያለመ መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጉቼ ጉሌ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ ዩኒቨርሲቲው በምርምር ሥራዎችና በማህበረሰብ አገልግሎት የአካባቢውን ማህበረሰብ በተሻለ መልኩ ተጠቃሚ ለማድረግ ግብ አስቀምጦ እየሰራ ነው። በተለይ ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ዕድሎችን አስፍቶ ለመጠቀም የተመራማሪዎችን አቅም ማሳደግ ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ለእዚህም የምርምር ስራዎቹንና የማህበረሰብ አገልግሎቶቹን ለማጎልበት ከአገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ መሰል ተቋማት ጭምር ትብብርና ትስስሩን ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ በዩኒቨርሲቲው የሚገኙ ተመራማሪዎችን አቅም በማሳደግና ከዓለም አቀፍ መሰል ተቋማት ጋር ትስስሩን በማጎልበት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው በምርምርና በማህብረሰብ አገልግሎቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ ነው።   በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ ከ84 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ 54 የምርምር ሥራዎችን እንዲሁም 70 የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። በዚህም ከ1 ሚሊዮን በላይ የአካባቢውን ማህበረሰብ በቀጥታና በተዘዋዋሪ መንገድ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ የዛሬው መድረክም የተለያዩ ምርምሮች ውጤታማነትን በጋራ ገምግሞ የተሻለ አቅጣጫ ለመያዝና ለቀጣይ ዓመት መሰል ሥራዎች ተሞክሮ ለመቀመር ጠቃሚ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ተመራማሪዎች እና መምህራን ተገኝተዋል።    
በተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ምቹ አገልግሎት አግኝተናል - ተገልጋዮች
Jun 17, 2026 965
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ በተደረገው የተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰራር ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በይፋ ተመርቆ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል፡፡ ይህ ዘመናዊ አሠራር ነዋሪዎች ወደ ተለያዩ የመንግሥት ቢሮዎች መሄድ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት አካባቢ ሆነው ጉዳያቸውን በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ መፈጸም እንዲችሉ ምቹ ዕድል ፈጥሯል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች እንደገለጹት፤ አዲሱ የዲጂታል ተንቀሳቃሽ መሶብ አሠራር ቀደም ሲል የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችና እንግልቶች ያስቀረ ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል አቤል አለማየሁ እንደገለጸው የአገልግሎት የነዋሪነት መታወቂያውን በተንቀሳቃሽ መሶብ በ10 ደቂቃ ውስጥ ማሳደስ መቻሉን ተናግሯል።   ማንኛውንም አገልግሎት በአንድ ቦታ ማግኘት መቻሉ ጊዜን ለመቆጠብ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም አስታውቋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ መስፍን ተርፋ በበኩላቸው ቀደም ሲል መሰል ጉዳይ ለማስፈጸም ከሥራ ቀርተው ወደ ወረዳ ቢሮዎች በተደጋጋሚ ይመላለሱ እንደነበር አስታውሰዋል።   አሁን ግን በሻይ ዕረፍታቸው ወቅት በመምጣት በ5 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። የማዕከሉ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ባለሙያ ዳኜ መኮንን እንደተናገሩት፤ ከአስፈጻሚ ኤጀንሲዎች ጀምሮ እስከ ክፍለ ከተማና ወረዳ ያሉ መዋቅሮች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እርስ በእርስ በተናበበ ሁኔታ እየተሰራ ይገኛል።   መንገድ ፈንድና ፋይዳ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ባለሙያ እዝቹአለም ሲሳይ በበኩላቸው አሠራሩ ሕብረተሰቡ ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ቦታ እንዲያገኝ የሚረዳ ነው ብለዋል።   አገልግሎቱ ተንቀሳቃሽ መሆኑ ደግሞ ነዋሪዎች እግረ መንገዳቸውን እንዲጠቀሙበት ዕድል በመፍጠሩ፣ በርካታ ተገልጋዮች በሥራው ተደስተውና አመስግነው እየሄዱ መሆኑን አስታውቀዋል። ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት አስተባባሪ ዳኛቸው ተፈራ፤ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል።   አገልግሎቱ ሥራ ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በከተማዋ በሚገኙ ሁሉም ክፍለ ከተሞች በመዘዋወር አገልግሎት መስጠቱን አስታውቀዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ለመንግሥት ግዥ ሥርዓት ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል
Jun 17, 2026 631
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ለመንግሥት ግዥ ሥርዓት ውጤታማነት፣ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የፌዴራል ንብረትና ግዥ ባለስልጣን አስታወቀ። በበጀት ዓመቱ ባለፉት 11 ወራት ከ370 ቢሊዮን ብር በላይ በኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት መፈፀሙም ተጠቅሷል። የፌዴራል ንብረትና ግዥ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት 11 ወራት የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማጠናከርና የተቋማትን አቅም ለማጎልበት የአሰራር ሥርዓቶችን በማዘመን ረገድ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል። በአስተዳደር ስርዓቱ ውስጥ የአዋጅ መሻሻል እንዲሁም የመመርያዎቹ መውጣት ተከትሎ መዘጋጀት ያለባቸው መደበኛ የጨረታ ሰነዶችና ማንዋሎችን እንዲሁም የአሰራር ስርዓቶችን በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል። በዚህም 41 የሚሆኑ መደበኛ የጨረታ ሰነዶች በማዘጋጀት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ የተደረገ መሆኑን ገልጸው፤ 32ቱ የፌዴራል የመንግስት ግዥና ንብረት ሽያጭ የሚፈፀምባቸው መደበኛ የጨረታ ሰነዶች ሲስተም ውስጥ ተካተው ስራ ላይ ማዋል ተችሏል ብለዋል። በ2017 እና 2018 ሁሉም ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ግዥያቸውን የፈጸሙት በእቅዳቸው መሰረት እንደሆነ ገልፀው አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በየሩብ አመቱ እቅዳቸውን ማሻሻል የሚያስችል አማራጭ እንዳለው አንስተዋል። በበጀት ዓመቱ 367 የፌዴራል ባለበጀት መስሪያቤቶች ግዥያቸውን በኦንላይን እየፈፀሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ውስጥ ከ29 ሺህ በላይ ጨረታዎች ተካሂደው ከ370 ቢሊዮን ብር በላይ በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት የተፈጸመ ሲሆን፣ ይህም ያልታቀደ ግዥን በማስቀረት የሕዝብና የመንግሥትን ሀብት ከብክነት ለመጠበቅ ትልቅ እገዛ አድርጓል ብለዋል። የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓት የተገልጋዮችን የጊዜ ብክነትና አላስፈላጊ የትራንስፖርት ወጪን በማስቀረት፣ ባሉበት ቦታ ሆነው የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ አስችሏልም ብለዋል። ይህ አሰራር ከሰዎች ንክኪ ነፃ በመሆኑ ለአቅራቢዎች፣ ለተወዳዳሪዎችና ለግዢ ፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የጎላ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን አስገንዝበዋል። መረጃን በቀላሉ ለሁሉም ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑም ተጠያቂነትን በማስፈን ብልሹ አሰራርን በከፍተኛ ደረጃ ለመከላከል የሚያስችል ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ለመንግሥት ግዥ ሥርዓት ውጤታማነት፣ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን አብራርተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስራዎችን በማጠናከር ተጠቃሚዎችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬትም ሥርዓቱን በክልሎች የማስጀመር ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
ስፖርት
ደቡብ አፍሪካ ከቼክ ሪፐብሊክ ጋር አቻ ተለያይታለች
Jun 18, 2026 163
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ አንድ ሁለተኛ መርሐ ግብር ቼክ ሪፐብሊክ እና ደቡብ አፍሪካ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ማምሻውን በአትላንታ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማይክል ሳዲሌክ በስድስተኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ጎል ቼክ ሪፐብሊክን መሪ አድርጓል። ቴብሆ ሞክዌና በ83ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ባሳረፋት ግብ ደቡብ አፍሪካ አቻ ሆናለች። በጨዋታው ደቡብ አፍሪካ የተሻለ ብልጫ ነበራት። ደቡብ አፍሪካ በዓለም ዋንጫው የመጀመሪያ ነጥቧን አግኝታለች። ቼክ ሪፐብሊክም በተመሳሳይ የመጀመሪያ ነጥቧን አሳክታለች። ደቡብ አፍሪካ ወደ ጥሎ ማለፉ የመግባት ተስፋዋን ለማለምለም በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኮሪያ ሪፐብሊክን ማሸነፍ ይኖርባታል። በዚሁ ምድብ ሜክሲኮ ከኮሪያ ሪፐብሊክ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በጓድላሃራ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሁለቱ ሀገራት የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸውን ማሸነፋቸው የሚታወቅ ሲሆን አሸናፊው ቡድን ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ያረጋግጣል።
የአፍሪካ የዓለም ዋንጫ የተሳትፎ ታሪክ፤ ከአብዱልራህማን ፋውዚ ታሪካዊ ጎሎች እስከ ሞሮኮ አስደናቂ ገድል
Jun 18, 2026 177
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የዓለም ዋንጫ ጉዞ የጽናት፣ የድንቅ ድሎችና የታሪክ ለውጥ ተምሳሌት ነው። አህጉሪቱ ጥቂት ዕድሎችን ለማግኘት ከነበረባት ፈታኝ ጅማሮ ተነስታ፣ ዛሬ በዓለም እግር ኳስ ውስጥ ተፅእኖ ፈጣሪ ሆና ብቅ ብላለች ። በዓለም ዋንጫ መጀመሪያዎቹ አሥርት ዓመታት አፍሪካ በቅኝ አገዛዝ እና በፊፋ የኮታ መድብ ኢ-ፍትሃዊነት ምክንያት የመሳተፍ ዕድሏ በጣም ጠባብ ነበር። ይሁን እንጂ እ.አ.አ በ1934 በጣልያን በተካሄደው ሁለተኛው የዓለም ዋንጫ ግብፅ ተሳትፎ በማድረግ የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሀገር በመሆን ታሪክ ሰራች።   በወቅቱ ከሀንጋሪ ጋር ተጫውታ 4 ለ 2 በሆነ ውጤት ብትሸነፍም የአፍሪካን ስም በዓለም መድረክ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስጠራች ሀገር ሆና ተመዝግባለች። አብዱልራህማን ፋውዚ በጨዋታው ለግብጽ ሁለቱንም ግቦች በማስቆጠር በዓለም ዋንጫው ግብ ማስቆጠር የቻለ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተጫዋች ሆኗል። አብዱልራህማን ፋውዚ በዚህ ጨዋታ ላይ ሶስተኛ ግብ አስቆጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ ዳኛው በስህተት ከጨዋታ ውጪ (Offside) በማለት ሽረውታል። ያ ግብ ቢጸድቅ ኖሮ በዓለም ዋንጫ ታሪክ የመጀመሪያውን ሀትሪክ (በአንድ ጨዋታ ሶስት ግብ) ያስቆጠረ አፍሪካዊም ይሆን ነበር። ከዚያ በኋላ አፍሪካ ወደ መድረኩ ዳግም ለመመለስ እስከ 1970 (እ.አ.አ) መጠበቅ ነበረባት።   ሞሮኮ እ.አ.አ በ1970 በሜክሲኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው ዘጠነኛ የዓለም ዋንጫ በመሳተፍ ከግብጽ ቀጥሎ ሁለተኛዋ የአፍሪካ ሀገር ሆናለች። እ.አ.አ በ1978 በአርጀንቲና የተካሄደው 11ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ አፍሪካ ታሪክ የጻፈችበት ነበር። በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው ቱኒዚያ ሜክሲኮን 3 ለ 1 በማሸነፍ የአፍሪካን የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ድል አስመዝግባለች። እ.አ.አ በ1982 በስፔን አስተናጋጅነት በተካሄደው 12ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ተሳትፋ የነበረችው አልጄሪያ በወቅቱ ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን የነበረውን ጀርመንን (በወቅቱ ምዕራብ ጀርመን) 2 ለ 1 በማሸነፍ ያስመዘገበችው ውጤት ዓለም ያልጠበቀው ነበር። በጣልያን እ.አ.አ በ1990 በተካሄደው 14ኛው የዓለም ዋንጫ ካሜሮን በመጀመሪያ ጨዋታዋ አርጀንቲናን 1 ለ 0 ያሸነፈችበት ድል በእግር ኳስ አፍቃሪያን ላይ ግርምትን የፈጠረ ክስተት ሆኖ አልፏል።   ታዋቂው የካሜሮን አጥቂ ሮጀር ሚላ በ38 ዓመቱ ግብ በማስቆጠር አንጋፋው የአፍሪካ ተጫዋች መሆን ችሏል። ካሜሩን በወቅቱ የሩብ ፍፃሜ (Quarter-finals) ደረጃ ላይ በመድረስ የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሀገር በመሆን ታሪክ ሰራች። የማይበገሩት አንበሶች በወቅቱ በሩብ ፍጻሜ በእንግሊዝ 3 ለ 2 ተሸንፈው ግማሽ ፍጻሜ መግባት ባይችሉም በውድድሩ ላይ ስኬታማ ግስጋሴ አድርገዋል። እ.አ.አ በ2002 በጃፓን እና ኮሪያ ሪፐብሊክ ጣምራ አዘጋጅነት የተካሄደው 17ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ተካሄዷል። ሴኔጋል በመጀመሪያ ጨዋታዋ የወቅቱን የውድድሩን አሸናፊ ፈረንሳይ (የ1998 ሻምፒዮን) 1 ለ 0 በመርታት ያስመዘገበችው ድል ዓለምን ጉድ አሰኝቷል። ፓፓ ቡባ ዲዮፕ ግቧን ያስቆጠረው ተጫዋች ነው። ሴኔጋል በፈረንሳይ ድል ሳትገታ እስከ ሩብ ፍጻሜ መጓዝ ብትችልም በቱርኪዬ 1 ለ 0 ተሸንፋ አራት ውስጥ መግባት አልቻለችም። እ.አ.አ በ2010 ደቡብ አፍሪካ 19ኛውን የፊፋ ዓለም ዋንጫ ያዘጋጀች ሲሆን ይህም በአፍሪካ ምድር የተካሄደ የመጀመሪያው ዓለም ዋንጫ መሆኑ አዲስ ታሪክ እንዲጻፍ አስችሏል። ጋና አህጉሪቱን ወክላ እስከ ሩብ ፍፃሜ ብትጓዝም በኡራጓዩ ተጫዋች ሉዊስ ሱዋሬዝ የዕጅ ኳስ ጥፋትና በጭማሪ ሰዓት በባከነ ፍፁም ቅጣት ምት ምክንያት ለግማሽ ፍፃሜ ሳትበቃ ቀርታለች። በጋና እና ኡራጓይ መካከል የተደረገው ጨዋታ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ አንድ ለአንድ ተጠናቆ ነበር። ይህን ተከትሎ 30 ደቂቃ ተጨመረ። የጭማሪው ሰዓት ሊያልቅ ጥቂት ሰከንዶች ብቻ ሲቀሩ (በ120ኛው ደቂቃ ላይ) ጋና ድንቅ የማጥቃት እንቅቃሴ አድርጋለች። የጋናው ተጫዋች ዶሚኒክ አዲያህ በግንባሩ የገጫት ኳስ ወደ ኡራጓይ መረብ ውስጥ እየገባች ሳለ፣ የኡራጓዩ አጥቂ ሉዊስ ሱዋሬዝ (Luis Suárez) ልክ እንደ ግብ ጠባቂ በመዝለል ኳሷን በሁለት እጆቹ በመንካት አወጣት። ይህንን ተከትሎ ዳኛው ለሱዋሬዝ የቀይ ካርድ በመስጠት ከሜዳ ሲያሰናብቱት፣ ለጋና ደግሞ ወሳኝ የፍፁም ቅጣት ምት (Penalty) ሰጡ።   መላው የአፍሪካ አህጉር እና ስታዲየሙ ውስጥ የነበሩ ደጋፊዎች ታሪክ ሊሰራ መሆኑን እርግጠኛ ሆነው ጨፈሩ። ፍፁም ቅጣት ምቱን ለመምታት የጋናው ኮከብ አሳሞአ ጊያን ቀረበ። ነገር ግን የመታው ኳስ የጎሉን አግዳሚ (Crossbar) መትቶ ወደ ውጪ ወጣ። በዚህ ሰዓት ቀይ ካርድ አይቶ ወደ መልበሻ ክፍል እየተጓዘ የነበረው ሉዊስ ሱዋሬዝ፣ ኳሷ መውጣቷን ሲያይ በደስታ ሲዘልና ሲጨፍር በካሜራ ታይቷል። ይህ ድርጊቱ ለአፍሪካውያን ትልቅ ቁጭትና ንዴት የፈጠረ ነበር። ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቆ ወደ መለያ ምት ሲያመራ፣ ጋና 4 ለ 2 በሆነ ውጤት ተሸነፈች። ኡራጓይ ወደ ግማሽ ፍፃሜ ስትሰናዳ፣ የጋና እና የመላው አፍሪካ የዓለም ዋንጫ ህልም ሳይሳካ ቀረ። ይህ ክስተት የጋናን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን ልብ የሰበረ ነበር። አፍሪካውያን በዚህ ክስተት አንገታቸውን ደፍተው አልቀሩም። እ.አ.አ በ2022 በኳታር አስተናጋጅነት በተካሄደው 22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ሞሮኮ ተአምር ሰሪ ሀገር ሆነች። የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን (የአትላስ አንበሶች) ሳይጠበቁ ስፔንን እና ፖርቱጋልን አሸንፈው በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ግማሽ ፍፃሜ (Semi-final) ደረሱ። ይህም ሞሮኮ ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሀገር በመሆን አዲስ ታሪክ እንድትጽፍ አስችሏታል። በግማሽ ፍጻሜው በፈረንሳይ እንዲሁም በደረጃ ጨዋታው በክሮሺያ ተሸንፋ አራተኛ ደረጃን ይዞ ብታጠናቅቅም አፍሪካን ያኮራ ደማቅ ታሪክ ጽፋለች። ይህ የሞሮኮ ድል የአፍሪካውያንን የይቻላል መንፈስ ከፍ ያደረገ ክስተት ሆኗል።   በውድድሩ የ96 ዓመታት ታሪክ የዘንድሮውን ጨምሮ 14 የአፍሪካ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ላይ ተሳትፈዋል። ካሜሮን ስምንት ጊዜ በመሳተፍ ቀዳሚውን ስፍራ ይዛለች። ሞሮኮ እና ቱኒዚያ በተመሳሳይ ሰባት ጊዜ ተሳትፎ አድርገዋል። ናይጄሪያ ስድስት ጊዜ በመድረኩ ላይ ስትሳተፍ አልጄሪያ እና ጋና በተመሳሳይ አምስት ጊዜ የመሳተፍ እድል አግኝተዋል። ግብጽ፣ ሴኔጋል፣ ኮትዲቯር እና ደቡብ አፍሪካ በተመሳሳይ አራት ጊዜ ተሳትፎ ሲያደርጉ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አንድ ጊዜ ተሳትፋለች። አንጎላ፣ ቶጎ እና ኬፕቨርዴ በተመሳሳይ የአንድ አንድ ጊዜ ተሳትፎ ያላቸው ሀገራት ናቸው። የደሴቲቷ ሀገር በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ታሪካዊ ተሳትፎዋን የምታደርግ ሲሆን ይህም በውድድሩ የተሳተፈች 14ኛ ሀገር ያደርጋታል። 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል። በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ 10 የአፍሪካ ሀገራት ይሳተፋሉ። በዚህም መሰረት ሞሮኮ፣ ሴኔጋል፣ ግብፅ፣ ኮትዲቯር፣ አልጄሪያ፣ ቱኒዚያ፣ ጋና፣ ኬፕቨርዴ እና ደቡብ አፍሪካ በቀጥታ ያለፉ የአፍሪካ ሀገራት ናቸው። በአንጻሩ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን በክፍለ አህጉራዊ የማጣሪያ ውድድር (Play-off) የጃማይካ አቻዋን በመርታት ለዓለም ዋንጫው ያለፈች 10ኛዋ የአፍሪካ ሀገር በመሆን አዲስ ታሪክ ሰርታለች። ዛሬ አፍሪካ በዓለም ዋንጫ ላይ ዝም ብላ "ለመሳተፍ" ብቻ ሳይሆን፣ ዋንጫውን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ ምድር ለማምጣት በፅናት ለመፋለም ተዘጋጅታለች።
የዓለም ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
Jun 18, 2026 260
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- በ23ኛ የፊፋ ዓለም ዋንጫ የስምንተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በምድብ ሁለት ቼክ ሪፐብሊክ ከደቡብ አፍሪካ ምሸት አንድ ሰዓት ላይ በአትላንታ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በምድቡ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ቼክ ሪፐብሊክ በደቡብ ኮሪያ 2 ለ 1፣ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ የ2 ለ 0 ሽንፈት አስተናግደዋል። ሀገራቱ ከሽንፈታቸው ለማገገም እና ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋቸውን ለማለምለም ሶስት ነጥብ ማግኘት ይጠበቅባቸዋል። በዚሁ ምድብ ሜክሲኮ ከኮሪያ ሪፐብሊክ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በጓድላሃራ ስታዲየም ይጫወታሉ። ከአዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሜክሲኮ በመክፈቻው ጨዋታ ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ኮሪያ ሪፐብሊክ ቼክ ሪፐብሊክን 2 ለ 1 ማሸነፏ ይታወሳል። አሸናፊው ሀገር ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ያረጋግጣል። በምድብ ሁለት ስዊዘርላንድ ከቦስኒያ ሄርዞጎቪና ከምሽቱ አራት ሰዓት በሎስ አንጀለስ ስታዲየም፣ ካናዳ ከኳታር ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በቢሲ ፕሌስ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ስዊዘርላንድ ከኳታር፣ ካናዳ ከቦስኒያ ሄርዞጎቪና በተመሳሳይ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታው ሀገራቱ የመጀመሪያ ድላቸውን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ነው።
በዓለም ዋንጫው አፍሪካዊቷ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከፖርቹጋል ጋር አቻ ተለያየች
Jun 18, 2026 274
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ 11 የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፖርቹጋል ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ውጤት ተጠናቋል። ትናንት ማምሻውን በሂውስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጆአኦ ኔቬስ በስድስተኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ፖርቹጋል መሪ ሆናለች። የመጀመሪያው አጋማሽ ማብቂያ ላይ አሮን ዊሳ ከመረብ ላይ ያሳረፈው ጎል ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አቻ አድርጓል። ዊሳ ለኮንጎ በዓለም ዋንጫ ታሪክ የመጀመሪያውን ጎል በማስቆጠር ታሪክ ሰርቷል። ፖርቹጋል ከፍተኛ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ብትወስድም ሁለቱ ቡድኖች ተቀራራቢ የግብ እድሎችን ፈጥረዋል። ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ጎሏን ከማስቆጠር ባለፈ የመጀመሪያ ነጥቧንም አግኝታለች። አፍሪካዊቷ ሀገር ከ52 ዓመታት በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫው መመለሷ ይታወቃል። የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት ፍሊክስ ሼሲኬዲ በስታዲየሙ ተገኝተው ጨዋታውን በመከታተል ቡድኑን አበረታተዋል። ዓለም ዋንጫውን ያነሳሉ ተብለው ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ፖርቹጋል ነጥብ ጥላለች። ስድስተኛ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን ያደረገው አምበሉ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ41 ዓመት ከ132 ቀናት በመጫወት በውድድሩ ታሪክ በአንጋፋው እድሜ የተሰለፈ ተጫዋች መሆን አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል።
አካባቢ ጥበቃ
በሸገር ከተማ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል
Jun 18, 2026 430
ሸገር፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት መደረጉን የከተማ አስተዳደሩ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ደጀኔ በቀለ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከዚህ ቀደም በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብሮች የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል፣ ለአፈርና ውሃ ጥበቃ እንዲሁም ለሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች ተገኝተዋል።   መርሃ ግብሩ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምርም ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። በ2015 ዓ.ም የከተማው የደን ሽፋን 11 በመቶ ብቻ እንደነበረ አስታውሰው ኅብረተሰቡን በማሳተፍ በተከናወኑ ሥራዎች በአሁኑ ወቅት የደን ሽፋኑን 21 በመቶ ማድረስ ተችሏል ብለዋል። በዘንድሮው መርሃ ግብር ለከተማዋ የአየር ንብረት ተስማሚ ለሆኑ የፍራፍሬ ዓይነቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱንም አስታውሰዋል። በዚህም መሠረት እንደ አፕል፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሎሚ ያሉ የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት ለተከላ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በአጠቃላይ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የፍራፍሬ ችግኞች ብቻ ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። ባለፉት ዓመታት የከተማዋ ነዋሪዎች በመኖሪያ አካባቢያቸው የፍራፍሬ ችግኞችን ተክለው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተከታታይ ሥልጠናዎች ሲሰጡ መቆየታቸውንም ጠቁመዋል።   በአሁኑ ወቅት ኅብረተሰቡ ከመንግሥት ጋር በመሆን በመንግሥትና በግል ይዞታዎች፣ እንዲሁም ለፍራፍሬና ለውበት ተስማሚ በሆኑ ቦታዎች ላይ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶችን በማዘጋጀት ላይ ይገኛልም ነው ያሉት።  
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በክረምት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ይተከላሉ
Jun 18, 2026 184
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በክረምት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። አረንጓዴ ዐሻራ መርሀግብር የተፈጥሮ ሚዛንን ለመጠበቅ ካለው ፋይዳ ባለፈ የምግብ ዋስትናንና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ታላቅ ሀገራዊ ግብንም ይዟል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም ካለፉት ሰባት ዓመታት ወዲህ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀግብርም ለችግኝ ተከላ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶ በመከናወኑ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መጥቷል። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል እና የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አንደኛ ሽናሌ እንደገለጹት፣ በክልሉ የተፈጥሮ ሚዛኑን የጠበቀ አረንጓዴ አካባቢን ዕውን በማድረግ በኩል ውጤት ተገኝቷል፡፡   በተለይ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ባለፉት ሰባት ዓመታት በተከናወኑ ተግባራት የተራቆተ መሬትን መልሶ በደን በመሸፈንና ምርታማነትን በማሳደግ በኩል ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል። በዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብርም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል ታቅዶ አስፈላጊው ዝግጅት በማድረግ ወደ ተግባር መገባቱን ነው የገለጹት። በዘንድሮ የበልግ ወቅትም የደን፣ የፍራፍሬ እና ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ኃላፊው አስታውሰዋል። ዘንድሮም ለመርሐ-ግብሩ ስኬት በተሰጠው ልዩ ትኩረት፤ በበልግ ወቅት ከተተከሉት በተጨማሪ በክረምት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተለያየ ጥቅም የሚሰጡ ችግኞች ለመትከል አስፈላጊው ቅድመ ዘግጅት መደረጉን አስታውሰዋል። ለእዚህም በክልሉ ባሉ ከ1ሺህ 200 በላይ ችግኝ ጣቢያዎች ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ነው የገለጹት። ችግኞቹ ለምግብነት የሚውሉ፣ የፍራፍሬ፣ ለጥምር ደን፣ ለውበትና ለጥላ ዛፍ የሚያገለግሉ መሆናቸውን ገልጸው፣ ለእንስሳት መኖ የሚውሉም መተከላቸውን ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀግብር ለችግኝ ተከላ የሚሆኑ ጉድጓዶችን በመቆፈር ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ590 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በዚህም የክልሉ የደን ሽፋን ከነበረበት 18 ነጥብ 9 ከመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 23 በመቶ መድረሱ ታውቋል።  
የኢትዮጵያን አስደናቂ የአረንጓዴ ዐሻራና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ሊተገብሩት ይገባል
Jun 18, 2026 223
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ተሞክሮ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ሊሰፋ እንደሚገባ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ኦፊሰር ቻርለስ አኮል ገለጹ። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የአካባቢ መራቆትን ለመግታትና የውሃ ሃብት ዘላቂነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤቶች እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ ባደረጉት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተመሳሳይ የ2018 የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ መጣሉን አስታውቀዋል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ኦፊሰር ቻርለስ አኮል ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብር የተጎዱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ እያደረገ የሚገኝ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘላቂ ውሃ አጠቃቀም ላይም መርሃ ግብሩ ትርጉም ያለው ውጤት እያመጣ መሆኑን ተመልክተናል ያሉት ኦፊሰሩ፤ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራና አካባቢ ጥበቃ ላይ የሚደነቅ ሥራ እያከናወነች ነው ብለዋል። የደን ሽፋንን ማሳደግ የውኃ ሀብትን በዘላቂነት ለመጠበቅ ተጨባጭ ማሳያ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን ለማሳደግ ፈጣንና ሁሉን አቀፍ ሥራዎች እየተገበረች መሆኑን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት።   የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ተሞክሮን ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሊተገበሩት እንደሚገባ ጠቁመው፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ተሞክሮ ወደ ሌሎች ሀገራት እንዲሰፋ እያደረጉት ያለውንም ጥረት አድንቀዋል። በአፍሪካ የአካባቢ ጥበቃን ለማሳለጥ “ታላቁ የአፍሪካ አረንጓዴ ግንብ” የተሰኘ መርሃ ግብር መኖሩን አስታውሰው፤ ይህን መርሃ ግብር ከኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ጋር ማቀናጀት ለአህጉራዊ አካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ብለዋል። የአረንጓዴ ልማቱን ማስፋፋት በአፍሪካ ያለውን የውሃና የመሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ከማሻሻሉ በላይ ለስራ እድል ፈጠራና ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
በመዲናዋ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለፍራፍሬ ችግኞች ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል
Jun 18, 2026 207
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ለዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የፍራፍሬ ተክሎችን በስፋት ያካተቱ አምስት ሚሊየን ችግኞች መዘጋጀታቸውን የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግርማ ሰይፉ ገለጹ። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ በተከታታይ ባከናወነችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር እስካሁን 48 ቢሊየን ችግኞችን መትከል ችላለች።   የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሀገራዊ ሕልሟ ጋር የተቆራኘ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበበት ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በቢሾፍቱ በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት፣ በዘንድሮው ዓመት ብቻ ስምንት ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምጧል። አባቶቻችን በአድዋ ላይ ታሪካዊ ገድል ፈጽመው ሀገር እንዳስረከቡን ሁሉ፣ የአሁኑ ትውልድም በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ሌላኛውን የአረንጓዴ አርበኝነት ገድል እየደገመ ይገኛል። ይህ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ የሚፈጥረው የአየር ንብረት ለውጥ የመቋቋም አቅምና የምግብ ሉዓላዊነት ስኬት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ሉዓላዊነቷ የተረጋገጠና የበለጸገች ሀገር ለማስረከብ ለተጀመረው ጉዞ እንደ ትልቅ ምሰሶ የሚቆጠር ነው። የአዲስ አበባ ከተማ የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግርማ ሰይፉ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በመዲናዋ ዘንድሮ ለሚከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የዝግጅት ሥራ ተጠናቋል። በአሁኑ ወቅትም የችግኝ ማፍላትና የቦታ መረጣ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በከተማዋ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች የፅድቀት ምጣኔ በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን ጠቁመው፣ በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት ያካተቱ አምስት ሚሊየን ችግኞች እንደሚተከሉ አስታውቀዋል። በመሆኑም ወጣቶች እና ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በዘንድሮው የችግኝ ተከላና እንክብካቤ ሥራ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።   በሱሱኒ ችግኝ ጣቢያ የዘር ብዜትና የችግኝ እንክብካቤ ባለሙያ ተሾመ ፉፋ እንደገለጹት በጣቢያው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርን ስኬታማ ለማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት መደረጉን አንስተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በጣቢያው አንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን ችግኞች ለተከላ ዝግጁ የተደረጉ ሲሆን በርካታ የተዳቀሉ የፍራፍሬ ዘር ችግኞች መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። ችግኞቹ ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ ተከታታይ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚያስፈልጋቸው የተናገሩት ደግሞ ሌላኛዋ ባለሙያ የሆኑት ፅጌ ነጋ ናቸው።   አረንጓዴ ዐሻራን ከግብ ለማድረስ ችግኝን መትከል ብቻ ሳይሆን ተገቢውን እንክብካቤ ማድረግም ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 9284
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 7285
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 6106
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 6012
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
 የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jun 15, 2026 1312
በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉የተራሮች ስር ፈርጥ - ወልዲያ የዛሬው የወፍ በረር ምልከታችን የሚጀምረው የተራሮች ስር ፈርጥ በሆነችው ወልዲያ ከተማ በመገኘት ነው። ከደሴ በ120 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውና በረጃጅም ተራሮች የተከበበችው ወልዲያ ከተማ ከነበረችበት ጉስቁልና ወጥታ አሁን ላይ በውበት ፈክታ ትገኛለች። በሳምንቱ በዚህች ከተማ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኮሪደር ልማቷንና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፤ ተዘዋውረውም ጎብኝተዋል። በተለያዩ ታሪካዊና ባህላዊ ትውፊቶች ስሟ ጎልቶ የሚጠራው ወልዲያ እንደ ከዋክብት ፈክታ እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር እየተስፋፉ መሆኑን አንስተው በቀጣይ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ትገሰግሳለች ብለዋል። 👉የሸደር አዳሪ ትምህርት ቤት የሚቀጥለው መዳረሻችን በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን አውበሬ ወረዳ ሼደር ከተማ አዲስ የተገነባውን አዳሪ ትምህርት ቤት መመረቅ ይሆኗል። የትምህርት ቤቱን ግንባታ መርቀው ስራ ያስጀመሩት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ናቸው። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው፤ በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋት የተማረ ትውልድ ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በ138 ሚሊየን ብር የተገነባው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ስራ መጀመሩ ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል። 👉የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የበረራ ቅኝታችን ቀጥሎ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በመስኖ እየለማ ያለ የስንዴ ምርት የመጎብኘት እድል አግኝተናል። በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል መሰብሰብ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። የግብርና ሜካናይዜሽንን በስፋት በመጠቀም እንዲሁም ፈጠራን በማከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ጥረቱ በተሳካ መልኩ መቀጠሉን አንስተዋል። 👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ዓለም አቀፍ ክስተት ነው። ችግሩ በተለይም በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ ይገኛል። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መጠን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ መፍትሄ ለመስጠት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። በዚህ ረገድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት በሚከናወኑ ሥራዎች በምርምር እያገዙ ናቸው። በሂደቱ ውጤታማነት ላይ የሚመክር መድረክ በሰመራ በተደረገበት ወቅት የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ችግሩን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት በምርምርና በማማከር እያገዙ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሰዎች ህገወጥ ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ለህብረተሰቡ እየሰጡ ናቸው። 👉የኢትዮጵያ እያመረተች ነው በአማራ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እና ሌሎችም በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለውጭ ምንዛሬ አይነተኛ የገቢ ምንጭ መሆን አስችሏል ብለዋል። 👉መሶብ በአርባ ምንጭ፣ ዲላ እና ነቀምቴ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት በዚህ ሳምንት አርባ ምንጭ፣ እና ዲላ ከተሞች ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። የመሶብ ማእከላቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል። የዲጅታል አሰራርን በማስፋት ለዜጎች ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። 👉ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩ ስለመሆኑ ያነሳል። በመሆኑም ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን አደራጅቷል። በመሆኑም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በእለቱ ድምፅ መስጠት ካልቻሉት መካከል የሰሜን ምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በፊት ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፃቸውን ሰጥተዋል። በተመሳሳይ በአፋር ክልል እና በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያዎች የሚገኙ ዜጎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል። 👉የመኸር እርሻ ንቅናቄ በሲዳማ ክልል የመኸር እርሻን በንቅናቄ በመምራት የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡና ገበያን የሚያረጋጉ የግብርና ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በንቅናቄ መድረኩ ርእሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት መሬት ጦሙን እንዳያድርና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ እንዲሁም ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠት ምርታማነቱን ማሳካት አስችሏል። ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል የበልግ ሰብልን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። ይህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ በማምረት ገበያን ለማረጋጋትና ለኢንደስትሪዎች ግብአት ለማቅረብ ያስችላል ነው የተባለው። በምርት ዘመኑ የተያዘውን እቅድ ለማሳካትም አመራሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር ለውጤቱ መትጋት እንዳለበትም በውይይቱ ተነስቷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምርጥ ዘር ብዜትን በዓይነት፣ በመጠንና በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ ተችሏል። ቢሮው በግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ እና በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዘር ብዜት ዕቅድ አፈጻጸምና ዝግጅት ላይ ያተኮረ የባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ እንደገለጹት፤ በክልሉ የምርጥ ዘርን በጥራትና በመጠን ለአርሶ አደሩ በወቅቱ በማድረስ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል። ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ለኢንዱስትሪዎች በቂ ግብዓትን ለማቅረብና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር አግዟል። ተግባሩን በማስቀጠልም በ2017/18 የምርት ዘመን በክልሉ ከ2 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ30 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ማምረት መቻሉንም ገልጸዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት
Jun 14, 2026 1156
በኢዜአ ዐይን …! በሙሴ መለሰ አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው።በዚህ ሂደት ደግሞ የኢትዮጵያ ድንቅ ስራ የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊትአውራሪነት ይጠቀሳል። መርሐ-ግብሩ የጋራ ነው በሚል ዕሳቤ በርካቶችን በንቃት አሳትፎ ለዓለም የሚደርስ የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ዐሳይቷል። የደን ሽፋን መጠንን አሳድጓል። ይህም በዓየር ንብረት ለውጥ ላይ የራሱን ሚና እያበረከተ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአረንጓዴ ዐሻራ ሚና ልቆ ይነሳል። ይህም የተራቆተ መሬትን ወደ ነበረበት ከመመለስ፣ የውኃ ሀብት አሥተዳደርን ምቹ ከማድረግ እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ጋር የሚያያዝ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብሩ በዕድሜ፣ በጾታ፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሥራ ዘርፎች፣ በኑሮ ደረጃ፣ በሐይማኖት ሳትለይ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች እንዲሳተፉበት በማድረጓ በዘርፉ ስኬታማ ጉዞ ላይ ናት። ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀት ከመሆን አልፎ ለጎረቤቶቿ ችግኝ በመለገስ መርሐ-ግብሩ እንዲስፋፋ እየተጋችም ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ሲናገሩ፤ አረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያ ትላልቅ ነገር አስባ፣ ትላልቅ ነገር ተልማ፣ ትላልቅ ነገር አቅዳ እና ሕዝቦቿን አስተባብራ ማሳካት እንደምትችል ለሌሎቹ ማሳያ ነው ማለታቸውም ከላይ ያነሳነውን ሐሳብ ያዳብረዋል። በተጨማሪም አረንጓዴ ዐሻራ በልዩ ትኩረት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሳይቆራረጥ እየተሠራ መሆኑን፤ በየዓመቱም በሚተከሉ ችግኞች ብዛት፣ በሚተከልበት መሬት ስፋት እና በሚሳተፉ ታታሪዎች ቁጥር እያደገ መሆኑን ያመላክታል። በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች እየወጡ በችግኝ ተከላ መሳተፋቸው የሀገርን የጋራ ራዕይ ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 5215
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 10036
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
ትንታኔዎች
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 1369
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ።   ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…! 
Jun 15, 2026 726
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 5215
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው?
Jun 12, 2026 1745
የጤና ነገር … በዮሐንስ ደርበው የሰው ልጅ ሊሻሻሉ በሚችሉ እና በማይችሉ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ለልብ ህመም ሊጋለጥ እንደሚችል የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የአዋቂ የልብ ሕክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ብርሃኑ ሞገስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የልብ ህመም ከተወሳሰብ ዘላቂ የጤና እክል እስከ ድንገተኛ ኅልፈት ያደርሳል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ሰዎች ማሻሻል በሚችሏቸው (ሞዲፋይብል) እና ማሻሻል በማይችሏቸው (ነን ሞዲፋይብል ወይም ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች) ለልብ ህመም ሊጋለጡ እንደሚችሉ ዶክተር ብርሃኑ ይገልጻሉ። መሻሻል ከሚችሉ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል፤ ከፍተኛ ጭንቀት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ ከፍተኛ የደም ግፊት ህመም (በአግባቡ መድኃኒቱ ካልተወሰደ)፣ተገቢ ያልሆነ የስብ ክምችት፣ ከፍተኛ ውፍረት (ክብደት)፣ በቂ እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ጤናማ አመጋገብ አለመኖር እንዲሁም አብዝቶ ስኳር፣ ጣፋጭና አልኮል መጠቀም የሚሉትን ይጠቅሳሉ፡፡ እንዲሁም ሰዎች ማሻሻል ከማይችሏቸው (ተፈጥሯዊ) አጋላጮች መካከል፤ በቤተሰብ የሚተላለፍ መኖሩን፣ በዕድሜ መጨመር የሚከሰት መሆኑን (ለምሳሌ፡- ወንድ ከ45 ሴት ከ55 ዓመት በላይ ሲሆናቸው ለልብ ህመም ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩን) እንዲሁም ወንዶ ከሴቶች በይበልጥ ለልብ ህመም ተጋላጭ የመሆናቸው አጋጣሚ ሰፊ ሊሆን እንደሚችልም አብራርተዋል፡፡ በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የልብ ህመም ምልክቶች የደረት ውጋት በግራ በኩል ወይም መሐል ላይ፣ ከወትሮው የተለየ ድካም፣ ትንፋሽ ማጠር፣ ከመደበኛው የተለየ የልብ ምት መኖር፣ የሰውነት በተለይም እግር አካባቢ እብጠት፣ ራስን መሳት እና ሳል የልብና ተያያዥ ህመም ምልክት ሊሆኑ እንደሚችሉ አብራርተዋል። የልብን ጤናን ለመጠበቅ በተቻለ መጠን ጤናማ አመጋገብን መከተል እንደሚገባ የሚመክሩት ዶክተር ብርሃኑ፤ አትክልት ማዘውተር፣ ምግብ ሲዘጋጅም ፈሳሽ ዘይት መጠቀም፣ ስኳር፣ ጨው እና ጣፋጭ ነገሮችን መገደብ ከተቻለም ማስወገድ እንደሚገባ ይመክራሉ፡፡ አካላዊ እንቅስቃሴ ማዘውተር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ይህም ብስክሌት መንዳት፣ በእግር እንቅስቃሴ ማድረግ፣ ዋና መዋኘት፣ እስከሚያልብ እና የልብ ምት እስከሚጨምር ብሎም እስከሚደክሙ የአካል ብቃት መሥራት የልብን ጤና ለመጠበቅ አስተዋጽዖ አለው ነው ያሉት፡፡ ጤናማ የሰውነት ክብደት እንዲኖር ማድረግ ተገቢ መሆኑን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ “ቦዲ ማስ ኢንዴክስ (ቢ ኤም አይ)” ከ18 ነጥብ 5 እስከ 25 እንዲሆን ይመከራል ብለዋል፡፡ ሲጋራ አለማጨስ፣ አልኮል አለመጠቀም፣ የስኳር ህመምና ከፍተኛ ደም ግፊት ካለም የመድኃኒት አወሳሰድን አለማስተጓጎል፣ አመጋገብ ላይ ስብ አለማብዛትና አብዝቶ አለመቀመጥ የልብ ህመምን ለመከላከል እንደሚያግዙ ነው ያስረዱት፡፡ ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በታች የሆኑ ጤናማ ሰዎች ከአንድ እስከ ሦስት ዓመት ባሉ ጊዜያት አንድ ጊዜ፣ ዕድሜያቸው ከ45 በላይ የሆኑ በየዓመቱ እንዲሁም የልብ ህመም ያለባቸው እንደሁኔታው በየጊዜው ክትትል እንዲያደርጉም መክረዋል፡፡ ሰዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እራሳቸውን ከልብ ህመም እንዲጠብቁ መክረው፤ ከዚህ ያለፈ ችግር ሲኖር ቶሎ የሕክምና ክትትል ማድረግ እና “ዛሬ ነገ” በማለት ጊዜ እያባከኑ ህመሙ ውስብስብ ደረጃ እስኪደርስ መጠበቅ እንደማይገባቸው አሳስበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ጤና #የልብ_ህመም
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 608
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 15583
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 8670
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 14442
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 83475
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 66433
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 46777
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 44349
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 33761
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 33241
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 32707
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 31963
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 83475
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 66433
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 46777
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 44349
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 10036
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 7540
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም