ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በቁርጠኝነት ከተሰራ ከተማ እና ሀገርን መገንባት እንደሚቻል አዲስ አበባ ማሳያ ናት - የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት 
Nov 8, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በቁርጠኝነት ከተሰራ ከተማ እና ሀገርን መገንባት እንደሚቻል አዲስ አበባ ማሳያ ናት ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ስኬት ለሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎች አርአያ እንደሚሆንም አመራር አባላቱ ገልጸዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኮሪደር፣ የወንዝ ዳር ልማት፣ የቤት ልማት እና አቅርቦት ስራዎችን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ መስጠፌ መሀመድ፤ በጉብኝቱ አዲስ አበባ የኢትዮጵያን ገጽታ ከፍ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎችን እያካሄደች መሆኗን ተመልክተናል ብለዋል።   በተለይም የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷን የሚያጸኑ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን አይተናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በአመራሩ ቁርጠኝነት ሀገር መለወጥ የሚያስችል መልካም እድል መኖሩን ያመላከተ ነው ብለዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው፤ በኦሮሚያ ክልልም ሆነ በአዲስ አበባ ያየናቸው የልማት ውጤቶች ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና ማማ ለማድረስ በትክክለኛው መስመር ላይ መሆናችንን አመላካች ነው ብለዋል።   የኢትዮጵያን ትልሞች ከዳር በማድረስ ተጨማሪ ስኬቶችን ለማስመዝገብ ዝግጁ ነን ሲሉም ገልጸዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መነቴ ሙንዲኖ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት ለሌሎች ከተሞችም ከፍተኛ ልምድ እንደሚሆን ተናግረዋል።   ልማትን ቀጣይነት ባለው መልኩ እያረጋገጡ ለመሄድ ተግባራዊ እርምጃዎችን በላቀ ደረጃ የምንወስድበት ጊዜ ነው ብለዋል።
በፕሪሚየር ሊጉ ዌስትሃም ዩናይትድ እና ኤቨርተን ድል ቀንቷቸዋል 
Nov 8, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ11ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች መካሄዳቸውን ቀጥለዋል። ማምሻውን በለንደን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዌስትሃም ዩናይትድ በርንሌይን 3 ለ 2 አሸንፏል። ካሉም ዊልሰን፣ ቶማስ ሱቼክ እና ካይል ዎከርስ-ፒተርስ የማሸነፊያ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ዚያን ፍሌሚንግ እና ጆሽ ኩለን ለበርንሌይ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ዌስትሃም በሊጉ ተከታታይ ድሉን ሲያስመዘግብ በአንጻሩ በርንሌይ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል።   በሌላኛው መርሃ ግብር ኤቨርተን ፉልሃምን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢድሪሳ ጌይ እና ማይክል ኪን ግቦቹን አስቆጥረዋል። ኤቨርተን ከሁለት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል። ፉልሃም በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል። መርሃ ግብሩ ምሽትም ቀጥሎ ሲውል ሰንደርላንድ ከሊጉ መሪ አርሰናል ከምሽቱ 2 ሰዓት ከ30፣ ቼልሲ ከዎልቭስ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት ችለናል - የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች 
Nov 8, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት መቻላቸውን የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም በሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በአዳማ ከተማ መሰጠቱ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ላይ ያጠነጠኑ ስልጠናዎችን ወስደዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ትናንት በአዳማ ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባ ባደረጉት ጉብኝት በግብርና እና ከተማ ልማት የተከናወኑ ስራዎችን ተመልክተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር ሙስጠፌ መሃመድ፤ የብልጽግና ፓርቲ ብዝሃ ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ በርካታ ድሎችን ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል። በግብርና ኢንዱስትሪ፣ በከተሞች ልማትና በቱሪዝም ዘርፎች የተደረጉ ሪፎርሞችና የተገኙ ውጤቶች የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር መሰረት መጣላቸውንም አንስተዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳደር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ኢትዮጵያ ያላት ጸጋዎች ከራሷ አልፎ ለሌሎች የሚተርፍ መሆኑን ያየንበት ነው ብለዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በነበራቸው ቆይታ በተለያዩ ዘርፎች ላይ እየተከናወኑ ስላሉ ስራዎችና ስለተገኙ ውጤቶች የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንም ነው የተናገሩት። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር ሙስጠፌ እንዳሉት፤ በመደመር እይታ በፈጠራና በፍጥነት ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው አልፋ ከዓለም አገራት ጋር ተወዳዳሪ የመሆን አቅም እንዳላትና ለዚህ ደግሞ አመራሩ በቁርጠኝነት እንዲሰራ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳደር ጥላሁን እንደተናገሩት፤ በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት ተችሏል።
በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለሀብቶች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል
Nov 8, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የአገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ መኖሩን የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ በዳዳ ገለጹ። በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ውስጥ ማቲዎስ መባ ኮስሞቲክስ ማኑፋክቸሪንግ የግል ድርጅት የኮስሞቲክስ ፋብሪካ ተመርቋል።   በዚሁ ወቅት የቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ በዳዳ እንዳሉት፤ የአገር ውስጥም ሆነ የውጪ ባለሀብቶች አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶች በተሟሉበት በዞኑ በመድሃኒትና በፋርማሲዩቲካል ዘርፎች በስፋት እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል። አሁን ላይ በልዩ ኢኮኖሚክ ዞኑ ባለሀብቶች በተለያየ የማምረት ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ገልጸው፤ አሁንም ተጨማሪ ባለሃብቶች በመምጣት በሚፈልጉት ዘርፍ ተሰማርተው እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ አሁን ላይ በቋሚና በጊዜያዊነት ለ4 ሺህ 700 በላይ ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ከውጪ የሚገቡ የመድሃኒትና የፋርማሲዩቲካል ምርቶችን ለመተካት የተለያዩ ኩባንያዎች መድሃኒት እያመረቱ መሆኑን ተናግረዋል።   ማቲዎስ መባ ኮስሞቲክስ ማኑፋክቸሪንግ የግል ድርጅት ባለቤትና ስራ አስፈጻሚ አቶ ማቲዎስ መባ በበኩላቸው፤ ፋብሪካው በመጀመሪያ ዙር በ100 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክቱን ማስጀመሩን ገልጸዋል። ፋብሪካው የኮስሞቲክስ ምርቶችን በአገር ውስጥ በማምረት ከውጪ የሚገባውን ምርት ለመተካት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ ለ260 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።
የሚታይ
በቁርጠኝነት ከተሰራ ከተማ እና ሀገርን መገንባት እንደሚቻል አዲስ አበባ ማሳያ ናት - የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት 
Nov 8, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በቁርጠኝነት ከተሰራ ከተማ እና ሀገርን መገንባት እንደሚቻል አዲስ አበባ ማሳያ ናት ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ስኬት ለሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎች አርአያ እንደሚሆንም አመራር አባላቱ ገልጸዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኮሪደር፣ የወንዝ ዳር ልማት፣ የቤት ልማት እና አቅርቦት ስራዎችን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ መስጠፌ መሀመድ፤ በጉብኝቱ አዲስ አበባ የኢትዮጵያን ገጽታ ከፍ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎችን እያካሄደች መሆኗን ተመልክተናል ብለዋል።   በተለይም የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷን የሚያጸኑ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን አይተናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በአመራሩ ቁርጠኝነት ሀገር መለወጥ የሚያስችል መልካም እድል መኖሩን ያመላከተ ነው ብለዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው፤ በኦሮሚያ ክልልም ሆነ በአዲስ አበባ ያየናቸው የልማት ውጤቶች ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና ማማ ለማድረስ በትክክለኛው መስመር ላይ መሆናችንን አመላካች ነው ብለዋል።   የኢትዮጵያን ትልሞች ከዳር በማድረስ ተጨማሪ ስኬቶችን ለማስመዝገብ ዝግጁ ነን ሲሉም ገልጸዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መነቴ ሙንዲኖ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት ለሌሎች ከተሞችም ከፍተኛ ልምድ እንደሚሆን ተናግረዋል።   ልማትን ቀጣይነት ባለው መልኩ እያረጋገጡ ለመሄድ ተግባራዊ እርምጃዎችን በላቀ ደረጃ የምንወስድበት ጊዜ ነው ብለዋል።
በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት ችለናል - የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች 
Nov 8, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት መቻላቸውን የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም በሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በአዳማ ከተማ መሰጠቱ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ላይ ያጠነጠኑ ስልጠናዎችን ወስደዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ትናንት በአዳማ ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባ ባደረጉት ጉብኝት በግብርና እና ከተማ ልማት የተከናወኑ ስራዎችን ተመልክተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር ሙስጠፌ መሃመድ፤ የብልጽግና ፓርቲ ብዝሃ ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ በርካታ ድሎችን ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል። በግብርና ኢንዱስትሪ፣ በከተሞች ልማትና በቱሪዝም ዘርፎች የተደረጉ ሪፎርሞችና የተገኙ ውጤቶች የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር መሰረት መጣላቸውንም አንስተዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳደር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ኢትዮጵያ ያላት ጸጋዎች ከራሷ አልፎ ለሌሎች የሚተርፍ መሆኑን ያየንበት ነው ብለዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በነበራቸው ቆይታ በተለያዩ ዘርፎች ላይ እየተከናወኑ ስላሉ ስራዎችና ስለተገኙ ውጤቶች የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንም ነው የተናገሩት። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር ሙስጠፌ እንዳሉት፤ በመደመር እይታ በፈጠራና በፍጥነት ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው አልፋ ከዓለም አገራት ጋር ተወዳዳሪ የመሆን አቅም እንዳላትና ለዚህ ደግሞ አመራሩ በቁርጠኝነት እንዲሰራ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳደር ጥላሁን እንደተናገሩት፤ በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት ተችሏል።
የኢትዮጵያና ጃፓን የዲፕሎማሲ ግንኙነት በዘርፈ ብዙ የትብብር መስኮች ተጠናክሮ ቀጥሏል  
Nov 8, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ጃፓን የዲፕሎማሲ ግንኙነት በዘርፈ ብዙ የትብብር መስኮች ተጠናክሮ መቀጠሉን በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂሮኖሪ ገለጹ። የጃፓን የባህል ቀን በዛሬው ዕለት የተለያዩ ሀገራት የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እና የተለያዩ ታዳሚዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተከብሯል።   በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂሮኖሪ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በሁለቱ አገራት መካከል በጋራ መግባባት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አለ። የጃፓን መንግሥት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የትምህርት ዕድል መስጠቱን አመልክተው፤ በየጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የሥልጠና ፕሮግራሞች አማካኝነት በርካታ ሰልጣኞች ዕድሉን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። የሀገራቱን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማሳደግ ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም አንስተዋል። ጃፓንና ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸው ከመሰረቱበት ጊዜ አንስቶ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። ይህም በአፍሪካ ከጃፓን የመጀመሪያዎቹ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች አንዱን እንደሚወክል ገልጸው፤ ግንኙነቱም በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚ፣ በባህላዊና ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። ጃፓን እንደ ትምህርት፣ ጤናና ግብርና ባሉ መስኮች የገንዘብና የቴክኒክ ትብብርን ማስፋፋቷን አንስተዋል። የጃፓንና ኢትዮጵያን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርም ጥረታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ገልጸዋል።   በባህልና እና ስፖርት ሚኒስቴር የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አህመድ መሀመድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያና ጃፓን ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ገልጸዋል። በዓሉ በኢትዮጵያና በጃፓን መካከል እያበበ ላለው ሕያው የባህል ግንኙነት ሁነኛ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም መሰል በዓላት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸው አመልክተዋል።
የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያስቀጥል እመርታዊ የዕይታ አቅም ፈጥሯል
Nov 8, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያስቀጥል እመርታዊ የዕይታ አቅም መፍጠሩን የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ስልጠና ተሳታፊዎች ገለጹ። ፓርቲው ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበትን አካታችና አቃፊ ምኅዳር በመፍጠር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም የሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰሞኑን በአዳማ ከተማ ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ሥልጠና በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል፡፡ ከፍተኛ አመራር አባላቱም ከስልጠናው በተጓዳኝ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የግብርና ስራዎችን ጎብኝተዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤሊያስ፤ ስልጠናው የኢትዮጵያን የማንሰራራት ዘመን በማጽናት የግብርና ኢንዱስትሪ ሽግግርን የሚያፋጥን ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት ነው ብለዋል። የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ፣ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ የኢንዱስትሪ ሽግግርን ማፋጠን የሚያስችል የአመራር ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። በቱሪዝም፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በኢንዱስትሪና ከተማ ልማትን ስራዎችም ተመጋጋቢ የኢኮኖሚ ዕድገት ማሳለጫ አቅሞች መሆናቸውንም ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ የመደመር መንግሥት ዕይታ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያስቀጥል አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል።   የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ሥልጠናም የኢትዮጵያን ዕድገት ለማስቀጠል የጠራ ግንዛቤን በመያዝ ወደ ተግባር የሚገባበት ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በቱሪዝም፣ በገጠርና ግብርና ሽግግር፣ ኢንዱስትሪ፣ ከተማ ዕድገትና የልማት መስክ አንኳር ጉዳዮች ላይ ተቀራራቢ ዕውቀትና ግንዛቤ የተገኘበት መሆኑን አንስተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበትን አካታችና አቃፊ ምኅዳር በመፍጠር የኢትዮጵያና ዜጎቿን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የመስክ ምልከታቸውም የብልፅግና ፓርቲ ከቃል የተሻገረ ተጨባጭ ስኬት ያስመዘገቡ የልማት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑና ማሳያ መሆናቸውን ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ሠለሞን፤ በአዳማ የስልጠና ቆይታቸው በቱሪዝም፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በአንዱስትሪና ከተማ ልማት ወሳኝ የኢኮኖሚ ዕድገት መስኮች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማላቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።   በስልጠናውም የሀገርን ሁለንተናዊ ዕድገት በተቀናጀና በተናበበ መልኩ ለመምራት ልምድና ተሞክሮ በመጋራት ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን አጽንቶ የሚያስቀጥል አቅም የተፈጠረበት መሆኑንም ተናግረዋል። በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሕመድ አሊ፤ በስልጠናው ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና አህትማማችነትን በማጠናከር የኢትዮጵያ ህብረት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።   በስልጠናውም የበለጸገችና የዜጎቿ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ከፍተኛ የአመራር ስምሪት የተሰጠበት መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ጸጋዎች በማልማት ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልጽግናን የሚያረጋግጥ የኢኮኖሚ አቅም እየተፈጠረ ነው
Nov 8, 2025 84
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ጸጋዎች በማልማት ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልጽግናን የሚያረጋግጥ የኢኮኖሚ አቅም እተፈጠረ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም የሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰሞኑን ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ስልጠና በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል፡፡ ከፍተኛ አመራር አባላቱም ከስልጠናው በተጓዳኝ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የግብርና ስራዎችን ጎብኝተዋል።   የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ በወሳኝ የኢኮኖሚ የልማት መስኮች በከፍተኛ የለውጥ ምህዋር ውስጥ እየተጓዘች እንደሚገኝ ገልጸዋል። የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ስልጠናም የኢትዮጵያ የስኬት አቅጣጫ በዕውቀትና ክህሎት መምራት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በተሳታፊ አመራሮች መካከልም ኢትዮጵያ በጸጋዋ ልክ ዕድገትና ብልጽግናዋን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ቁጭትና የልምድ ልውውጥ የተፈጠረበት መድረክ መሆኑንም አንስተዋል። በስልጠናውም በወሳኝ የኢኮኖሚ ልማት መስኮች የመደመር መንግስት ዕይታ በዘርፎች እመርታ ላይ ንድፈ ሃሳብን ከተግባር በማቀናጀት የኢትዮጵያን የዕድገት አቅጣጫ ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። በጋምቤላ ክልል የአኝዋ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኝኬው ጊሎ፤ ስልጠናው የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሻሻል ዕውቀትና አቅም የተገነባበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።   በቀጣይም በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ዕድገት የተገኙ የዕውቀትና ክህሎት ተሞክሮዎችን ወደተግባር መቀየር የሚያስችል አቅም የተፈጠረበት መሆኑን ተናግረዋል። ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል የተሰባሰቡ ስልጠናው ተሳታፊዎችም ሕብረብሔራዊ አንድነትን በማስጠበቅ ሀገራዊ ዕድገትን በማስቀጠል የበለጠ የእርስ በእርስ መተዋወቂይ መድረክ መሆኑም ገልጸዋል። የአፋር ክልል የዳያስፖራ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጋሳ ሁመድ፡ ስልጠናው የኢትዮጵያን የማንሰራራት ዘመን የሚያረጋግጥ አቅም የተፈጠረበት ነው ብለዋል።   በቀጣይም በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ምርታማነት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል ልምድና ተሞክሮ የተጋሩበት መድረክ መሆኑንም ገልጸዋል። በስልጠና እና የመስክ ምልከታውም የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ማፋጠን የሚያስችል ሕብረ ብሔራዊነት በማስጠበቅ የአመለካከትና የተግባር አንድነት ተግባቦት የተፈጠረበት መሆኑን አስረድተዋል። በስልጠናው ላይ ሁሉም የክልልና ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ አመራር አባላት ተወካዮች መሳተፋቸውም ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን በማጠናከር የጋራ ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መሰረት መሆኑን ተናግረዋል። በኦሮሚያ ክልል የወሊሶ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ለማ ጋሩምሳ፤ በስልጠናውም ሀገራዊ አንድነትና የጋራ የልማት አፈፃጸም አቅሞች የተፈጠረበት መድረክ መሆኑን ተናግረዋል።   ስልጠናው ኢትዮጵያ የያዘችውን የብልጽግና ጉዞ ለማጽናት ልምድና ተሞክሮ የተጋሩበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። በመስክ ምልከታቸውም በንድፈ ሃሳብ ከወሰዱት ስልጠና ጋር የተዛመደ ተጨባጭ የልማት ስኬት እየተመዘገበ መሆኑን መሬት ላይ መመልከታቸውን አንስተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት ችለናል - የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች 
Nov 8, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት መቻላቸውን የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም በሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በአዳማ ከተማ መሰጠቱ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ላይ ያጠነጠኑ ስልጠናዎችን ወስደዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ትናንት በአዳማ ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባ ባደረጉት ጉብኝት በግብርና እና ከተማ ልማት የተከናወኑ ስራዎችን ተመልክተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር ሙስጠፌ መሃመድ፤ የብልጽግና ፓርቲ ብዝሃ ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ በርካታ ድሎችን ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል። በግብርና ኢንዱስትሪ፣ በከተሞች ልማትና በቱሪዝም ዘርፎች የተደረጉ ሪፎርሞችና የተገኙ ውጤቶች የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር መሰረት መጣላቸውንም አንስተዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳደር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ኢትዮጵያ ያላት ጸጋዎች ከራሷ አልፎ ለሌሎች የሚተርፍ መሆኑን ያየንበት ነው ብለዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በነበራቸው ቆይታ በተለያዩ ዘርፎች ላይ እየተከናወኑ ስላሉ ስራዎችና ስለተገኙ ውጤቶች የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንም ነው የተናገሩት። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር ሙስጠፌ እንዳሉት፤ በመደመር እይታ በፈጠራና በፍጥነት ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው አልፋ ከዓለም አገራት ጋር ተወዳዳሪ የመሆን አቅም እንዳላትና ለዚህ ደግሞ አመራሩ በቁርጠኝነት እንዲሰራ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳደር ጥላሁን እንደተናገሩት፤ በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት ተችሏል።
ምሩቃን የፖሊስ አባላትና መኮንኖች ለህገ መንግሥቱ ታማኝ በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)  
Nov 8, 2025 123
ቡልቡላ ፤ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ):- ምሩቃን የፖሊስ አባላትና መኮንኖች ለህገ መንግሥቱ ታማኝ በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) አስገነዘቡ፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በቡልቡላ መሰረታዊ ወታደራዊ የፖሊስ ማሰልጠኛ ማዕከል ያሰለጠናቸውን የመጀመሪያ ዙር ምልምል የፖሊስ ሰልጣኞችንና 2ኛ ዙር እጩ መኮንኖችን ዛሬ አስመርቋል፡፡   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የልማት እቅዶችን ተግባራዊ ለማድረግና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ይጠይቃል፡፡ በተለይም የፖሊስ አባላት በታማኝነትና በቅንነት ህዝባቸውን በማገልገል ሙያዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ የፖሊስ አባላት ማህበረሰቡን በስነ ምግባር በማገልገል የክልሉን ሰላምና ልማት ማጠናከር ላይ ያላቸውን ድርሻ እንዲያጠናክሩም አሳስበዋል፡፡ የዛሬ ምሩቃን የፖሊስ አባላትና መኮንኖችም ለሰንደቅ ዓላማና ለህገ መንግሥት ታማኝ በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡም አስገንዝበዋል፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ በበኩላቸው ኮሚሽኑ የክልሉን ፖሊስ በሰው ኃይል በማደራጀት ለክልሉ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡   ምሩቃንም የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል የፖሊስ አገልግሎትን በመተግበር ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል፡፡ በስልጠና ቆይታቸው ያገኙትን ለተልዕኮ ዝግጁ የሚያደርጉ ክህሎት በመጠቀም በታማኝነት ማህበረሰቡን ማገልገል እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ድሪባ መኮንን እንደገለፁት የተጀመሩ የልማት እቅዶችን እውን ለማድረግ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ ለዚህም የሁለቱን አጎራባች ክልሎችን ዘላቂ ሰላም በማስጠበቅ የማህበረሰቡን የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ ጉዞን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። "ኮሌጁ በሀገር አቀፍ ደረጃ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር ጎሳዬ ከበደ ናቸው፡፡ ኮሌጁ ክልላዊ ትስስርን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጋር በመተባበር የፖሊስ አካላትን ሲያሰለጥን መቆየቱን አስታውሰው ዘላቂ ሰላም ለማስፈን የሚያግዙ ስልጠናዎች በብቃት እንደተሰጠም ተናግረዋል፡፡
ብልጽግና የዜጎችን ተጠቃሚነት በማሳደግ በሃሳብ ጥራት ላይ የተመሰረተ ተጨባጭ ስኬት እያስመዘገበ  ነው 
Nov 8, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦የብልጽግና ፓርቲ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ በሃሳብ ጥራት ላይ የተመሰረተ ተጨባጭ ስኬት እያስመዘገበ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም በሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ስልጠና በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፤ ስልጠናው በርካታ አዳዲስ የልማት ዕውቀትና እሳቤዎች የተሰጡበት ነው ብለዋል። በስልጠናውም ላይ የኢትዮጵያን ቀጣይ አቅጣጫና አሁናዊ የልማት አቋም ታሳቢ በማድረግ አቅምና ክህሎትን የሚገነቡ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች መቅረባቸውን ገልጸዋል። የብልፅግና ፓርቲ የሃሳብ ጥራት ያለው፣ የገባውን ቃል በተግባር የሚፈጽም የሁለንተናዊ ዕድገት መሰረት እየሆነ መምጣቱንም ገልጸዋል። ፓርቲው ሕብረ ብሔራዊነትን የሚያስጠብቅና ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበት የሀገራዊ አንድነት መገለጫ እንደሆነም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያን የልማት ጉዞ ወደላቀ ከፍታ ለማሸጋገር በተከናወኑ ተግባራት በቱሪዝም፣ በገጠርና ከተማ፣ በኢንዱስትሪ የልማት መስኮች እመርታዊ ስኬት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የዕድገት አለኝታ ተብለው በተለዩ የኢኮኖሚ መስኮች የሀገርን ሁለንተናዊ ብልፅግና ማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ስኬት መመዝገቡን አስረድተዋል። ስልጠናው የኢትዮጵያን ጸጋዎች ጥቅም ላይ ለማዋል ከፍተኛ ቁጭትና ተነሳሽነትን የፈጠረ ወሳኝ የአቅም ግንባታ መድረክ መሆኑን አንስተዋል። የአፋር ክልል የማዕድን ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ መሐመድ ሁመድ፤ በስልጠናው የመደመር መንግሥትን የዘርፎች የመልማት ዕምቅ አቅም መገንዘባቸውን ገልጸዋል።   ስልጠናው የዘርፎችን የተሰናሰለና ተመጋጋቢ የልማት አቅም ወደ ተግባር ለመቀየር የሚያስችል ዕውቀትና ክህሎት ያገኙበት መሆኑንም ጠቁመዋል። የጋምቤላ ክልል ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኳንግ ዑኳይ፤ የብልፅግና ፓርቲ ስልጠና ለቀጣይ ስራቸው ዕውቀትና ክህሎትን የቀሰሙበትና ዘመኑን የዋጀ መሆኑን ገልጸዋል።   በቆይታቸውም የተሻለ አፈፃጸም ካስመዘገቡ የፌደራል ተቋማትና ክልሎች ልምድና ተሞክሮ መቅሰማቸውን አንስተዋል።
የኢትዮጵያና ጃፓን የዲፕሎማሲ ግንኙነት በዘርፈ ብዙ የትብብር መስኮች ተጠናክሮ ቀጥሏል  
Nov 8, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ጃፓን የዲፕሎማሲ ግንኙነት በዘርፈ ብዙ የትብብር መስኮች ተጠናክሮ መቀጠሉን በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂሮኖሪ ገለጹ። የጃፓን የባህል ቀን በዛሬው ዕለት የተለያዩ ሀገራት የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እና የተለያዩ ታዳሚዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተከብሯል።   በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂሮኖሪ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በሁለቱ አገራት መካከል በጋራ መግባባት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አለ። የጃፓን መንግሥት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የትምህርት ዕድል መስጠቱን አመልክተው፤ በየጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የሥልጠና ፕሮግራሞች አማካኝነት በርካታ ሰልጣኞች ዕድሉን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። የሀገራቱን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማሳደግ ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም አንስተዋል። ጃፓንና ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸው ከመሰረቱበት ጊዜ አንስቶ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። ይህም በአፍሪካ ከጃፓን የመጀመሪያዎቹ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች አንዱን እንደሚወክል ገልጸው፤ ግንኙነቱም በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚ፣ በባህላዊና ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። ጃፓን እንደ ትምህርት፣ ጤናና ግብርና ባሉ መስኮች የገንዘብና የቴክኒክ ትብብርን ማስፋፋቷን አንስተዋል። የጃፓንና ኢትዮጵያን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርም ጥረታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ገልጸዋል።   በባህልና እና ስፖርት ሚኒስቴር የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አህመድ መሀመድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያና ጃፓን ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ገልጸዋል። በዓሉ በኢትዮጵያና በጃፓን መካከል እያበበ ላለው ሕያው የባህል ግንኙነት ሁነኛ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም መሰል በዓላት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸው አመልክተዋል።
 ጽንፈኛውን ቡድን ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም እንታገላለን
Nov 8, 2025 66
ወልዲያ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡- በተለያዩ አጋጣሚዎች እገታና ዘረፋ እየፈፀመ ያለውን ጽንፈኛ ቡድን ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም እንታገላለን ሲሉ የአሽከርካሪዎች ማህበራት ተናገሩ። "የባዳና የባንዳን ሴራ በማምከን አንፀባረቂ ድሎችን እናስመዘግባለን "በሚል መሪ ሀሳብ በወልዲያ ከተማ ከባጃጅ፣ ከታክሲና ሌሎች የተሽከርካሪ ማህበራት ጋር በሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ላይ ውይይት ተካሂዷል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ፋሲካው መስፍን ፣አቶ ምህረቴ መኮንን እና ወጣት ጋሻው አለማየሁ በሰጡት አስተያየት፤ አሁን ላይ ሕዝቡ በሰላም መስራት፣ ወጥቶ መግባትና የልማት ስራዎችን ለማሳካት በከፍተኛ ፍላጎትና ተነሳሽነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሕዝቡ ፍላጎትና ተግባራዊ እንቅስቃሴ ይህ ቢሆንም እየተሹለከለከ አገታ፣ ዘረፋና ግድያ እየፈፀመ ያለው ጽንፈኛ ቡድን ችግር እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።   በመሆኑም በተለያዩ አጋጣሚዎች እገታና ዘረፋ እየፈፀመ ያለውን ጽንፈኛ ቡድን ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም እንታገላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የውይይት መድረኩን የመሩት በመከላከያ ሰራዊት የ11ኛ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሜጀር ጄኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌ፤ ጽንፈኛው ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመተባበር የህዝብን ሰላም ለማናጋትና የሀገርን ጥቅም ለማሳጣት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም የህዝብ ጠላትና የልማት ጸር የሆነውን ጽንፈኛ ቡድን በመከታተል ጠንካራ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸው እርምጃው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። በዚህ ጥረት ውስጥ የህዝቡን ትብብርና እገዛ አድንቀው፤ በወንጀል እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ አካላትን በማጋለጥና መረጃ በመስጠት ጭምር የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የምሥራቅ ዕዝ በየተሰማራበት የግዳጅ ቀጣና ተልዕኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መወጣቱን አጠናክሮ ቀጥሏል-ሜጀር ጄነራል ፍቃዱ ፀጋዬ
Nov 8, 2025 88
ጅግጅጋ፤ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡-የምሥራቅ ዕዝ በየተሰማራበት የግዳጅ ቀጣና ተልዕኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መወጣቱን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠሉን የዕዙ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄነራል ፍቃዱ ፀጋዬ ገለጹ። ዕዙ በማሰልጠኛ ማዕከሉ የአቅም ግንባታ ማጠናከርያ ስልጠና የሰጣቸውን ወታደሮች አስመርቋል።   በምረቃው ሥነ- ሥርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የምሥራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀnራል ፍቃዱ ፀጋዬ እንደገለጹት፤ ዕዙ የሀገርን ሉዓላዊነትና የሕዝቦችን ደሕንነት በላቀ ብቃትና ጀግንነት እያስጠበቀ ይገኛል። በተለይ ዕዙ በተለያዩ ጊዜ የተሰጠውን ተልዕኮና ግዳጅ በላቀ ብቃት ስኬታማ አፈፃፀም እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። የሕዝቦችን ሰላምና ደሕንነት የሚነሱ ጽንፈኞችንና ተላላኪዎችን በመደምሰስ አኩሪ ገድል መፈፀሙንም አንስተዋል። የምሥራቅ ዕዝ በየተሰማራበት የግዳጅ ቀጣና እና አካባቢ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት፣ ቁርጠኝነትና ጀግንነት መወጣቱን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠሉን ሜጀር ጄነራል ፍቃዱ ፀጋዬ አረጋግጠዋል።   ስልጠናውም የሠራዊቱ አባላት በማንኛውም ጊዜና በየትኛውም ቦታ ለሚፈጠር የፀጥታ ስጋት ተገቢውን ምላሽ መስጠት የሚያስችልና የተሟላ የዝግጁነት ቁመና የገነባ ነው ሲሉ ገልጸዋል። የሠራዊቱ አባላትም በማዕከሉ ያገኙትን ክሕሎት በመጠቀም ሕገ መንግስታዊና ተቋማዊ ተልዕኮን በጀግንነት ታጥቀውና ሕዝባዊ ባሕሪ ተላብሰው መወጣት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የምሥራቅ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል አዛዥ ኮለኔል አሊ ሰዒድ በበኩላቸው፤ ተመራቁ የሰራዊቱ አባላት ከዕዙ የተለያዩ ኮሮች የተውጣጡ መሆናቸወን ተናግረዋል።   የሠራዊቱ አባላት በማዕከሉ ቆይታቸው ዘመናዊ ወታደራዊ ዕውቀትና ጥበብ የቀሰሙ መሆናቸውን ጠቁመው፥ በስልጠና ቆይታቸው ያገኙት እውቀትም የሚሰጣቸውን ግዳጅ በብቃት እንዲወጡ የሚያግዝ ነው ብለዋል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የዕዙ ከፍተኛ መኮንኖች፣የሶማሌና ሐረሪ ክልል የፖሊስ ኮሚሽነሮችና ሌሎች አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያስቀጥል እመርታዊ የዕይታ አቅም ፈጥሯል
Nov 8, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያስቀጥል እመርታዊ የዕይታ አቅም መፍጠሩን የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ስልጠና ተሳታፊዎች ገለጹ። ፓርቲው ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበትን አካታችና አቃፊ ምኅዳር በመፍጠር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም የሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰሞኑን በአዳማ ከተማ ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ሥልጠና በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል፡፡ ከፍተኛ አመራር አባላቱም ከስልጠናው በተጓዳኝ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የግብርና ስራዎችን ጎብኝተዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤሊያስ፤ ስልጠናው የኢትዮጵያን የማንሰራራት ዘመን በማጽናት የግብርና ኢንዱስትሪ ሽግግርን የሚያፋጥን ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት ነው ብለዋል። የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ፣ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ የኢንዱስትሪ ሽግግርን ማፋጠን የሚያስችል የአመራር ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። በቱሪዝም፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በኢንዱስትሪና ከተማ ልማትን ስራዎችም ተመጋጋቢ የኢኮኖሚ ዕድገት ማሳለጫ አቅሞች መሆናቸውንም ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ የመደመር መንግሥት ዕይታ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያስቀጥል አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል።   የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ሥልጠናም የኢትዮጵያን ዕድገት ለማስቀጠል የጠራ ግንዛቤን በመያዝ ወደ ተግባር የሚገባበት ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በቱሪዝም፣ በገጠርና ግብርና ሽግግር፣ ኢንዱስትሪ፣ ከተማ ዕድገትና የልማት መስክ አንኳር ጉዳዮች ላይ ተቀራራቢ ዕውቀትና ግንዛቤ የተገኘበት መሆኑን አንስተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበትን አካታችና አቃፊ ምኅዳር በመፍጠር የኢትዮጵያና ዜጎቿን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የመስክ ምልከታቸውም የብልፅግና ፓርቲ ከቃል የተሻገረ ተጨባጭ ስኬት ያስመዘገቡ የልማት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑና ማሳያ መሆናቸውን ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ሠለሞን፤ በአዳማ የስልጠና ቆይታቸው በቱሪዝም፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በአንዱስትሪና ከተማ ልማት ወሳኝ የኢኮኖሚ ዕድገት መስኮች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማላቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።   በስልጠናውም የሀገርን ሁለንተናዊ ዕድገት በተቀናጀና በተናበበ መልኩ ለመምራት ልምድና ተሞክሮ በመጋራት ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን አጽንቶ የሚያስቀጥል አቅም የተፈጠረበት መሆኑንም ተናግረዋል። በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሕመድ አሊ፤ በስልጠናው ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና አህትማማችነትን በማጠናከር የኢትዮጵያ ህብረት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።   በስልጠናውም የበለጸገችና የዜጎቿ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ከፍተኛ የአመራር ስምሪት የተሰጠበት መሆኑንም ገልጸዋል።
ፖለቲካ
በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት ችለናል - የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች 
Nov 8, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት መቻላቸውን የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም በሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በአዳማ ከተማ መሰጠቱ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ላይ ያጠነጠኑ ስልጠናዎችን ወስደዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ትናንት በአዳማ ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባ ባደረጉት ጉብኝት በግብርና እና ከተማ ልማት የተከናወኑ ስራዎችን ተመልክተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር ሙስጠፌ መሃመድ፤ የብልጽግና ፓርቲ ብዝሃ ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ በርካታ ድሎችን ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል። በግብርና ኢንዱስትሪ፣ በከተሞች ልማትና በቱሪዝም ዘርፎች የተደረጉ ሪፎርሞችና የተገኙ ውጤቶች የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር መሰረት መጣላቸውንም አንስተዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳደር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ኢትዮጵያ ያላት ጸጋዎች ከራሷ አልፎ ለሌሎች የሚተርፍ መሆኑን ያየንበት ነው ብለዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በነበራቸው ቆይታ በተለያዩ ዘርፎች ላይ እየተከናወኑ ስላሉ ስራዎችና ስለተገኙ ውጤቶች የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንም ነው የተናገሩት። የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር ሙስጠፌ እንዳሉት፤ በመደመር እይታ በፈጠራና በፍጥነት ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው አልፋ ከዓለም አገራት ጋር ተወዳዳሪ የመሆን አቅም እንዳላትና ለዚህ ደግሞ አመራሩ በቁርጠኝነት እንዲሰራ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳደር ጥላሁን እንደተናገሩት፤ በመደመር መንግሥት ዕይታ በዘርፎች ላይ የመጣውን እመርታዊ ለውጥ በተጨባጭ ማየት ተችሏል።
ምሩቃን የፖሊስ አባላትና መኮንኖች ለህገ መንግሥቱ ታማኝ በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)  
Nov 8, 2025 123
ቡልቡላ ፤ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ):- ምሩቃን የፖሊስ አባላትና መኮንኖች ለህገ መንግሥቱ ታማኝ በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) አስገነዘቡ፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በቡልቡላ መሰረታዊ ወታደራዊ የፖሊስ ማሰልጠኛ ማዕከል ያሰለጠናቸውን የመጀመሪያ ዙር ምልምል የፖሊስ ሰልጣኞችንና 2ኛ ዙር እጩ መኮንኖችን ዛሬ አስመርቋል፡፡   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የልማት እቅዶችን ተግባራዊ ለማድረግና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ይጠይቃል፡፡ በተለይም የፖሊስ አባላት በታማኝነትና በቅንነት ህዝባቸውን በማገልገል ሙያዊ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ የፖሊስ አባላት ማህበረሰቡን በስነ ምግባር በማገልገል የክልሉን ሰላምና ልማት ማጠናከር ላይ ያላቸውን ድርሻ እንዲያጠናክሩም አሳስበዋል፡፡ የዛሬ ምሩቃን የፖሊስ አባላትና መኮንኖችም ለሰንደቅ ዓላማና ለህገ መንግሥት ታማኝ በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡም አስገንዝበዋል፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ በበኩላቸው ኮሚሽኑ የክልሉን ፖሊስ በሰው ኃይል በማደራጀት ለክልሉ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡   ምሩቃንም የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል የፖሊስ አገልግሎትን በመተግበር ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል፡፡ በስልጠና ቆይታቸው ያገኙትን ለተልዕኮ ዝግጁ የሚያደርጉ ክህሎት በመጠቀም በታማኝነት ማህበረሰቡን ማገልገል እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ድሪባ መኮንን እንደገለፁት የተጀመሩ የልማት እቅዶችን እውን ለማድረግ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ ለዚህም የሁለቱን አጎራባች ክልሎችን ዘላቂ ሰላም በማስጠበቅ የማህበረሰቡን የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ ጉዞን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። "ኮሌጁ በሀገር አቀፍ ደረጃ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር ጎሳዬ ከበደ ናቸው፡፡ ኮሌጁ ክልላዊ ትስስርን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጋር በመተባበር የፖሊስ አካላትን ሲያሰለጥን መቆየቱን አስታውሰው ዘላቂ ሰላም ለማስፈን የሚያግዙ ስልጠናዎች በብቃት እንደተሰጠም ተናግረዋል፡፡
ብልጽግና የዜጎችን ተጠቃሚነት በማሳደግ በሃሳብ ጥራት ላይ የተመሰረተ ተጨባጭ ስኬት እያስመዘገበ  ነው 
Nov 8, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦የብልጽግና ፓርቲ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ በሃሳብ ጥራት ላይ የተመሰረተ ተጨባጭ ስኬት እያስመዘገበ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም በሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ስልጠና በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፤ ስልጠናው በርካታ አዳዲስ የልማት ዕውቀትና እሳቤዎች የተሰጡበት ነው ብለዋል። በስልጠናውም ላይ የኢትዮጵያን ቀጣይ አቅጣጫና አሁናዊ የልማት አቋም ታሳቢ በማድረግ አቅምና ክህሎትን የሚገነቡ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች መቅረባቸውን ገልጸዋል። የብልፅግና ፓርቲ የሃሳብ ጥራት ያለው፣ የገባውን ቃል በተግባር የሚፈጽም የሁለንተናዊ ዕድገት መሰረት እየሆነ መምጣቱንም ገልጸዋል። ፓርቲው ሕብረ ብሔራዊነትን የሚያስጠብቅና ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበት የሀገራዊ አንድነት መገለጫ እንደሆነም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያን የልማት ጉዞ ወደላቀ ከፍታ ለማሸጋገር በተከናወኑ ተግባራት በቱሪዝም፣ በገጠርና ከተማ፣ በኢንዱስትሪ የልማት መስኮች እመርታዊ ስኬት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የዕድገት አለኝታ ተብለው በተለዩ የኢኮኖሚ መስኮች የሀገርን ሁለንተናዊ ብልፅግና ማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ስኬት መመዝገቡን አስረድተዋል። ስልጠናው የኢትዮጵያን ጸጋዎች ጥቅም ላይ ለማዋል ከፍተኛ ቁጭትና ተነሳሽነትን የፈጠረ ወሳኝ የአቅም ግንባታ መድረክ መሆኑን አንስተዋል። የአፋር ክልል የማዕድን ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ መሐመድ ሁመድ፤ በስልጠናው የመደመር መንግሥትን የዘርፎች የመልማት ዕምቅ አቅም መገንዘባቸውን ገልጸዋል።   ስልጠናው የዘርፎችን የተሰናሰለና ተመጋጋቢ የልማት አቅም ወደ ተግባር ለመቀየር የሚያስችል ዕውቀትና ክህሎት ያገኙበት መሆኑንም ጠቁመዋል። የጋምቤላ ክልል ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኳንግ ዑኳይ፤ የብልፅግና ፓርቲ ስልጠና ለቀጣይ ስራቸው ዕውቀትና ክህሎትን የቀሰሙበትና ዘመኑን የዋጀ መሆኑን ገልጸዋል።   በቆይታቸውም የተሻለ አፈፃጸም ካስመዘገቡ የፌደራል ተቋማትና ክልሎች ልምድና ተሞክሮ መቅሰማቸውን አንስተዋል።
የኢትዮጵያና ጃፓን የዲፕሎማሲ ግንኙነት በዘርፈ ብዙ የትብብር መስኮች ተጠናክሮ ቀጥሏል  
Nov 8, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ጃፓን የዲፕሎማሲ ግንኙነት በዘርፈ ብዙ የትብብር መስኮች ተጠናክሮ መቀጠሉን በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂሮኖሪ ገለጹ። የጃፓን የባህል ቀን በዛሬው ዕለት የተለያዩ ሀገራት የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እና የተለያዩ ታዳሚዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተከብሯል።   በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂሮኖሪ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በሁለቱ አገራት መካከል በጋራ መግባባት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አለ። የጃፓን መንግሥት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የትምህርት ዕድል መስጠቱን አመልክተው፤ በየጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የሥልጠና ፕሮግራሞች አማካኝነት በርካታ ሰልጣኞች ዕድሉን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። የሀገራቱን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማሳደግ ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም አንስተዋል። ጃፓንና ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸው ከመሰረቱበት ጊዜ አንስቶ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። ይህም በአፍሪካ ከጃፓን የመጀመሪያዎቹ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች አንዱን እንደሚወክል ገልጸው፤ ግንኙነቱም በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚ፣ በባህላዊና ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። ጃፓን እንደ ትምህርት፣ ጤናና ግብርና ባሉ መስኮች የገንዘብና የቴክኒክ ትብብርን ማስፋፋቷን አንስተዋል። የጃፓንና ኢትዮጵያን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርም ጥረታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ገልጸዋል።   በባህልና እና ስፖርት ሚኒስቴር የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አህመድ መሀመድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያና ጃፓን ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ገልጸዋል። በዓሉ በኢትዮጵያና በጃፓን መካከል እያበበ ላለው ሕያው የባህል ግንኙነት ሁነኛ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም መሰል በዓላት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸው አመልክተዋል።
 ጽንፈኛውን ቡድን ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም እንታገላለን
Nov 8, 2025 66
ወልዲያ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡- በተለያዩ አጋጣሚዎች እገታና ዘረፋ እየፈፀመ ያለውን ጽንፈኛ ቡድን ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም እንታገላለን ሲሉ የአሽከርካሪዎች ማህበራት ተናገሩ። "የባዳና የባንዳን ሴራ በማምከን አንፀባረቂ ድሎችን እናስመዘግባለን "በሚል መሪ ሀሳብ በወልዲያ ከተማ ከባጃጅ፣ ከታክሲና ሌሎች የተሽከርካሪ ማህበራት ጋር በሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ላይ ውይይት ተካሂዷል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ፋሲካው መስፍን ፣አቶ ምህረቴ መኮንን እና ወጣት ጋሻው አለማየሁ በሰጡት አስተያየት፤ አሁን ላይ ሕዝቡ በሰላም መስራት፣ ወጥቶ መግባትና የልማት ስራዎችን ለማሳካት በከፍተኛ ፍላጎትና ተነሳሽነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሕዝቡ ፍላጎትና ተግባራዊ እንቅስቃሴ ይህ ቢሆንም እየተሹለከለከ አገታ፣ ዘረፋና ግድያ እየፈፀመ ያለው ጽንፈኛ ቡድን ችግር እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።   በመሆኑም በተለያዩ አጋጣሚዎች እገታና ዘረፋ እየፈፀመ ያለውን ጽንፈኛ ቡድን ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም እንታገላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የውይይት መድረኩን የመሩት በመከላከያ ሰራዊት የ11ኛ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሜጀር ጄኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌ፤ ጽንፈኛው ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመተባበር የህዝብን ሰላም ለማናጋትና የሀገርን ጥቅም ለማሳጣት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም የህዝብ ጠላትና የልማት ጸር የሆነውን ጽንፈኛ ቡድን በመከታተል ጠንካራ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸው እርምጃው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። በዚህ ጥረት ውስጥ የህዝቡን ትብብርና እገዛ አድንቀው፤ በወንጀል እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ አካላትን በማጋለጥና መረጃ በመስጠት ጭምር የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የምሥራቅ ዕዝ በየተሰማራበት የግዳጅ ቀጣና ተልዕኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መወጣቱን አጠናክሮ ቀጥሏል-ሜጀር ጄነራል ፍቃዱ ፀጋዬ
Nov 8, 2025 88
ጅግጅጋ፤ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡-የምሥራቅ ዕዝ በየተሰማራበት የግዳጅ ቀጣና ተልዕኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መወጣቱን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠሉን የዕዙ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄነራል ፍቃዱ ፀጋዬ ገለጹ። ዕዙ በማሰልጠኛ ማዕከሉ የአቅም ግንባታ ማጠናከርያ ስልጠና የሰጣቸውን ወታደሮች አስመርቋል።   በምረቃው ሥነ- ሥርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የምሥራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀnራል ፍቃዱ ፀጋዬ እንደገለጹት፤ ዕዙ የሀገርን ሉዓላዊነትና የሕዝቦችን ደሕንነት በላቀ ብቃትና ጀግንነት እያስጠበቀ ይገኛል። በተለይ ዕዙ በተለያዩ ጊዜ የተሰጠውን ተልዕኮና ግዳጅ በላቀ ብቃት ስኬታማ አፈፃፀም እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። የሕዝቦችን ሰላምና ደሕንነት የሚነሱ ጽንፈኞችንና ተላላኪዎችን በመደምሰስ አኩሪ ገድል መፈፀሙንም አንስተዋል። የምሥራቅ ዕዝ በየተሰማራበት የግዳጅ ቀጣና እና አካባቢ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት፣ ቁርጠኝነትና ጀግንነት መወጣቱን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠሉን ሜጀር ጄነራል ፍቃዱ ፀጋዬ አረጋግጠዋል።   ስልጠናውም የሠራዊቱ አባላት በማንኛውም ጊዜና በየትኛውም ቦታ ለሚፈጠር የፀጥታ ስጋት ተገቢውን ምላሽ መስጠት የሚያስችልና የተሟላ የዝግጁነት ቁመና የገነባ ነው ሲሉ ገልጸዋል። የሠራዊቱ አባላትም በማዕከሉ ያገኙትን ክሕሎት በመጠቀም ሕገ መንግስታዊና ተቋማዊ ተልዕኮን በጀግንነት ታጥቀውና ሕዝባዊ ባሕሪ ተላብሰው መወጣት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የምሥራቅ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል አዛዥ ኮለኔል አሊ ሰዒድ በበኩላቸው፤ ተመራቁ የሰራዊቱ አባላት ከዕዙ የተለያዩ ኮሮች የተውጣጡ መሆናቸወን ተናግረዋል።   የሠራዊቱ አባላት በማዕከሉ ቆይታቸው ዘመናዊ ወታደራዊ ዕውቀትና ጥበብ የቀሰሙ መሆናቸውን ጠቁመው፥ በስልጠና ቆይታቸው ያገኙት እውቀትም የሚሰጣቸውን ግዳጅ በብቃት እንዲወጡ የሚያግዝ ነው ብለዋል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የዕዙ ከፍተኛ መኮንኖች፣የሶማሌና ሐረሪ ክልል የፖሊስ ኮሚሽነሮችና ሌሎች አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያስቀጥል እመርታዊ የዕይታ አቅም ፈጥሯል
Nov 8, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያስቀጥል እመርታዊ የዕይታ አቅም መፍጠሩን የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ስልጠና ተሳታፊዎች ገለጹ። ፓርቲው ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበትን አካታችና አቃፊ ምኅዳር በመፍጠር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም የሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰሞኑን በአዳማ ከተማ ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ሥልጠና በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል፡፡ ከፍተኛ አመራር አባላቱም ከስልጠናው በተጓዳኝ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የግብርና ስራዎችን ጎብኝተዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤሊያስ፤ ስልጠናው የኢትዮጵያን የማንሰራራት ዘመን በማጽናት የግብርና ኢንዱስትሪ ሽግግርን የሚያፋጥን ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት ነው ብለዋል። የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ፣ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማሳለጥ የኢንዱስትሪ ሽግግርን ማፋጠን የሚያስችል የአመራር ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። በቱሪዝም፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በኢንዱስትሪና ከተማ ልማትን ስራዎችም ተመጋጋቢ የኢኮኖሚ ዕድገት ማሳለጫ አቅሞች መሆናቸውንም ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ የመደመር መንግሥት ዕይታ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያስቀጥል አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል።   የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ሥልጠናም የኢትዮጵያን ዕድገት ለማስቀጠል የጠራ ግንዛቤን በመያዝ ወደ ተግባር የሚገባበት ዕውቀትና ክህሎት የተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በቱሪዝም፣ በገጠርና ግብርና ሽግግር፣ ኢንዱስትሪ፣ ከተማ ዕድገትና የልማት መስክ አንኳር ጉዳዮች ላይ ተቀራራቢ ዕውቀትና ግንዛቤ የተገኘበት መሆኑን አንስተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበትን አካታችና አቃፊ ምኅዳር በመፍጠር የኢትዮጵያና ዜጎቿን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የመስክ ምልከታቸውም የብልፅግና ፓርቲ ከቃል የተሻገረ ተጨባጭ ስኬት ያስመዘገቡ የልማት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑና ማሳያ መሆናቸውን ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ሠለሞን፤ በአዳማ የስልጠና ቆይታቸው በቱሪዝም፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በአንዱስትሪና ከተማ ልማት ወሳኝ የኢኮኖሚ ዕድገት መስኮች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማላቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።   በስልጠናውም የሀገርን ሁለንተናዊ ዕድገት በተቀናጀና በተናበበ መልኩ ለመምራት ልምድና ተሞክሮ በመጋራት ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን አጽንቶ የሚያስቀጥል አቅም የተፈጠረበት መሆኑንም ተናግረዋል። በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሕመድ አሊ፤ በስልጠናው ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና አህትማማችነትን በማጠናከር የኢትዮጵያ ህብረት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።   በስልጠናውም የበለጸገችና የዜጎቿ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ከፍተኛ የአመራር ስምሪት የተሰጠበት መሆኑንም ገልጸዋል።
ማህበራዊ
አብሮነትን ይበልጥ  በማጠናከር ሰላምን በዘላቂነት ማስጠበቅ የሁሉም ተግባር መሆን አለበት -አባ ገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች
Nov 8, 2025 54
ነቀምቴ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡ - አብሮነትና አንድነትን ይበልጥ በማጠናከር ሰላምን በዘላቂነት ማስጠበቅ የሁሉም ተግባር መሆን አለበት ሲሉ አባ ገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች ተናገሩ። በምስራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ ነገ የሚከበረውን የኢሬቻ በዓል ምክንያት በማድረግ ከተለያዩ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች የተውጣጡ አባ ገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች የተሳተፉበት የፓናል ውይይት ተካሄዷል።   በፓናል ውይይቱ ላይ የተገኙት አባ ገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች፤ የክልሉ ሕዝብ አንድነት እና አብሮነቱን ይበለጥ በማጠናከር ለሰላም ዘብ መቆም አለበት ብለዋል። የኦሮሞ አባ ገዳዎች ሕብረት ሰብሳቢ አባ ገዳ ወረቅና ተሬሳ እንዳመለከቱት፤ በየዓመቱ የሚከበረው ኢሬቻ የመከባበር ፣ የፍቅር እና የአንድነት በዓል ነው። በመሆኑም ሕዝቡ በዓሉን ሲያከብር ለአንድነት ትስስር ቅድሚያ በመስጠት መሆን እንዳለበት ጠቅሰው ፤ ሁሉም ለዘላቂ ሰላም መስፈን በጋራ መቆም እንዳለበት አመልክተዋል። አባ ገዳው፤ ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት ነው፤ በመተሳሰብ እና በመተባባር ዘላቂ ሰላም ለመገንባት በጋራ መረባረብ ይገባናል ብለዋል። በተለይ እርስ በእርስ በመከባበር እና በመቻቻል የተሻለች ሀገር ለመገንባት የሚደረገውን ጉዞ በሕብረት ማገዝ እንደሚገባም ተናግረዋል። ሌላው አባ ገዳ ሀይሉ ለገሰ በበኩላቸው ፤ ሕዝቡ አብሮነቱን ይበልጥ በማጠናከር ዘላቂ ሰላም ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ማገዝ አለበት ብለዋል። ኢሬቻ የሰላም እና የመከባበር በዓል ነው ያሉት አባ ገዳው፤ በዓሉ ሲከበር አንድነትን እና ሰላምን አጉልቶ ማሳየት እንደሚገባ ገልጸዋል። ሁሉም የሰላም ግንባታ እና ልማት ስራዎች ላይ ያለውን ድርሻ ማጠናከር እንዳለበት ያመለከቱት ደግሞ ሀደ ሲንቄ ትዕግስት ዲባባ ናቸው። ሕዝቡ አንድነቱን በማጎልበት ሀገርን ለማሳደግ እና ለማልማት የተጀመረውን ጉዞ ማጠናከር እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል የጡት ካንሰር  የግንዛቤ ማሳደጊያ ተግባር ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ነው
Nov 8, 2025 130
ሮቤ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦የጡት ካንሰር መነሻ ምክንያት እና መከላከያ መንገዶች የግንዛቤ ማሳደጊያ ስራ ላይ ትኩረት በማድረግ የእናቶችን ህይወት ለመታደግ ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከሩን የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል ገለጸ። ሆስፒታሉ የጡት ካንሰር በሽታ መነሻ ምክንያት እና መከላከያ መንገዶች ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ የውይይት መድረክ ዛሬ በሮቤ ከተማ አካሂዷል። በተለይም ለጡት ካንሰር በሚያጋልጡ ምክንያቶች ላይ ግንዛቤን በማሳደግ የእናቶችን ህይወት ለመታደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር መጠናከሩም ተገልጿል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል ዋና ዳይሬክተር ተባባሪ ፕሮፌሰር መሐመድአማን ማማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ሆስፒታሉ የካንሰር ህክምናን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ነው።   ጥቅምት ዓለም አቀፍ የጡት ካንሰር ግንዛቤ መፍጠሪያ ወር መሆኑን ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ይህንኑ ምክንያት በማድረግ ስለበሽታው ግንዛቤ የሚያስጨብጡ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። ሆስፒታሉ በተለያዩ አካባቢዎች ጊዜያዊ ጣቢያዎችን በማቋቋም ለህብረተሰቡ ከሚሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ በተጨማሪ ነፃ የምርመራና የምክር አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል። የሆስፒታሉ ባለሙያዎች በጡት ካንሰር ልየታና ቅድመ ምርመራ ላይ እያደረጉ የሚገኙት ሥራና የግንዛቤ መፍጠርያ ተግባራት የጥረቱ አካል መሆኑን አንስተዋል። በሆስፒታሉ የካንሰር ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር አዲስ ጉልላት፣ አብዛኛው የካንሰር ታማሚ የበሽታው ደረጃ ከፍ ካለና ከተሰራጨ በኋላ ለህክምና ስለሚመጡ ህክምናውን ከባድ እያደረገው መሆኑን አመልክተዋል።   የጡት ካንሰር በሽታ ቀድሞ ከተደረሰበት በሕክምና ሊድን እንደሚችል ያመለከቱት ዶክተር አዲስ፣ ለዚህም ህብረተሰቡ በቅድመ ልየታ ራሱን እንዲያውቅ ግንዛቤውን የማሳደግ ሥራ መስራት ይገባል ብለዋል። ህብረተሰቡ የአኗኗር ዘይቤውን በመቀየር በተለይ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግና ራሱን ከሱስ በማራቅ የካንሰር በሽታን መከላከል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰር በሽታ ሕክምናን በአግባቡ በመከታተል እንደሚድን የተናገሩት ደግሞ ከበሽታው በሕክምና እንደዳኑ የገለጹትና በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የሮቤ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ አስቴር ከተማ ናቸው። በሽታው ኖሮባቸው ተደብቀው የሚኖሩ እናቶች እንዳሉ የተናገሩት ወይዘሮ አስቴር፣ በጤና ተቋም ታክሞ መዳን እንደሚቻል ራሳቸውን በአብነት ጠቅሰዋል። ሴቶች በተለይም እናቶች "የካንስር በሽታ ዘመናዊ ህክምና አይወድም" በሚል የተሳሳተ ግንዛቤ ለጉዳት እየተዳረጉ መሆኑን መታዘባቸውን የገለጹት ደግሞ የከተማ ነዋሪ ወይዘሮ አለም ጸጋ ናቸው።   ስለበሽታው ባገኙት ግንዛቤ የካንሰር ቅድመ ምርመራ በማድረግ ራሳቸውን ለማወቅና ሌሎችንም ለማስተማር መነሳሳት እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ የሆኑ ነገሮችን ቀድሞ በመረዳት መከላከልና የህክምና ክትትል በማድረግ መዳን እንደሚቻል ከውይይቱ ያገኙትን ግንዛቤ ለሌሎች እንደሚያካፍሉ የገለጹት ደግሞ ሀደ ሲንቄ አባይ በቀለ ናቸው።   በሆስፒታሉ ዓለም አቀፍ የጡት ካንሰር የግንዛቤ መፍጠሪያ ወር በነፃ ምርመራና የምክር አገልግሎትን ጨምሮ በሌሎች መርሀ ግብሮች ተካሂዷል።
የዓመታት ጥያቄ ሆኖ የቆየው የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግራችን መፍትሄ አግኝቷል - የዋቻ ከተማ ነዋሪዎች
Nov 8, 2025 105
ቦንጋ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ካፋ ዞን የዋቻ ከተማ የዓመታት የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየው የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር መፍትሄ ማግኘቱን ነዋሪዎች ገለጹ። መንግስት የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችለውን የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያጎለብቱ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል። ከነዚህም ተግባራት መካከል በተለይ በገጠሩ አካባቢ የህክምና፣ የትምህርትና ሌሎች ተቋማትን በመገንባት የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን የማሳደግ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። ማህበራዊ ችግሮችን ከመፍታት አንፃርም በከተማና በገጠር ለሚገኙ ዜጎች የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ለዓመታት ለቆዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እየተሰጠ ይገኛል። በዚህም ተጠቃሚ ከሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል የዋቻ ከተማ ነዋሪዎች ተጠቃሽ ናቸው። በከተማዋ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ስራ መጀመር ለረጅም ዓመታት የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ ለቆየው ችግር መፍትሄን ይዞ እንደመጣም ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ገልፀዋል።   የከተማዋ ነዋሪ የሆኑን አቶ ጌታቸው አስፋው፤ ከዚህ ቀደም በንፁህ መጠጥ ውሃ እጦት ይቸገሩ እንደነበረ ጠቁመው በክልሉ መንግስት ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ፕሮጀክትም ችግሩን ሙሉ በሙሉ አስወግዶታል ብለዋል። ፕሮጀክቱ ከመመረቁ በፊት ምንም አይነት የቧንቧ ውሃ በከተማው እንዳልነበረና የጉድጓድና የምንጭ ውሃ ለመጠጥ ይጠቀሙ እንደነበረ የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ መላኩ ካፍትይመር ናቸው።   ችግራቸው እንዲፈታላቸው ለበርካታ ጊዜያት ጥያቄ ቢያቀርቡም ሰሚ አጥተው በጫና ውስጥ እንደቆዩና አሁን በለውጡ መንግስት የውሃ ፕሮጀክቱ ተገንብቶ ለአገልግሎት በመብቃቱ ትልቅ እፎይታ እንዳገኙ ተናግረዋል። ወይዘሮ የሺ መልካ በበኩላቸው አካባቢው የጉድጓድ ውሃን በቀላሉ ቆፍሮ ለማውጣት አስቸጋሪ መሆኑን ጠቁመው ፕሮጀክቱ ተመርቆ ስራ በመጀመሩ ለችግራቸው መፍትሄን እንዳመጣ ገልፀዋል።   ፕሮጀክቱ ለበርካታ ዓመታት የቆየውን የህብረተሰቡን ጥያቄ በመመለስ ትልቅ እፎይታን የፈጠረ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ሁነኛው ታደሰ ናቸው።   ይህም የለውጡ መንግስት የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየ ነው ብለዋል። የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ከ100 ሺህ በላይ ለሚሆን ነዋሪዎች አገልግሎት መስጠት የሚችል መሆኑን ገልፀው በቀጣይም አገልግሎቱ ያልተዳረሰባቸው ሰፈሮችን በመለየት የማስፋፊያ ስራ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ከተመረቀበት ጊዜ አንስቶ ያለ ምንም መቆራረጥ አገልግሎት እየሰጠ ነው ያሉት ነዋሪዎቹ ረጅም ጊዜ እንዲያገለግልም አስፈላጊውን ጥበቃና እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ይታወሳል።
 በዞኑ በክረምት ወራት የተከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአብሮነት እሴቶችንና የሰላም ግንባታን አጠናክሯል
Nov 8, 2025 75
አዶላ ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦ በጉጂ ዞን በክረምት ወራት የተከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአብሮነት እሴቶችንና የሰላም ግንባታን ማጠናከሩን የዞኑ ነዋሪዎች ገለፁ። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የዞኑ ነዋሪዎች እንደገለፁት አገልግሎቱ በዞኑ የህዝብ ለህዝብ የመረዳዳት፤ የሰላም ግንባታ፤ የልማትና የአብሮነት ባህላዊ እሴቶች እየተጠናከሩ እንዲመጡ እያደረገ ነው፡፡ በዞኑ የአዶላ ከተማ ነዋሪው አቶ ጌታቸው ጎልጃ፤ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ማህበራዊ ችግሮች እያቃለለና የመረዳዳት ባህልን እያሳደገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተለይም በበጎ ፈቃደኞች እየተተገበረ ያለውን መልካም ስራ በማስቀጠል ረገድ በአቅማችንን በመሳተፍ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ነባሩን የህዝብ ለህዝብ የመደጋገፍና የአብሮነት እሴት እያጎለበተ እንደመጣ የጠቆሙት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ገመቹ ቱሉ ናቸው፡፡ በጎ ፈቃድ ማህበራዊ ችግሮችን ከማቃለል ሌላ በሰላም ግንባታ፣ በልማት በሙያና በእውቀት ሽግግር የስራ ልምድና ባህልን እያሳደገ ይገኛል ብለዋል፡፡ በአዶላ ወረዳ የኦዳ ዶላ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ ዙፋን ተፈራ በበኩላቸው በእርጅና ምክንያት በፈረሰ ቤት ውስጥ ከ7 ልጆቻቸው ጋር ለዓመታት በክረምት ዝናብና በበጋ ጸሀይ እየተፈራረቀባቸው አስከፊ ህይወት እንዳሳለፉ ተናግረዋል፡፡ ''ዘንድሮ በበጎ ፈቃደኞች በተሰራልኝ ቤት ትልቁ ሸክሜ ተቃሎልኝ እየኖርኩ እገኛለሁ'' በማለት ለበጎ ፈቃደኞቹ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በጽህፈት ቤቱ የእቅድና በጀት ክትትል ኃላፊ አቶ ሙለታ መኩሪያ እንደተናገሩት፤ በክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በዋነኝነት በትምህርት፣ በጤና፣ በሰላም ግንባታ፣ በግብርናና በአረንጓዴ አሻራ ልማት በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል።   በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች 145 ኪሎ ሜትር የመንገድ፣ 206 የድልድይ፣ 89 የመማሪያ ክፍሎች፣ ለ6 ሺህ አረጋውያን የአዲስ ቤት ግንባታና እድሳት በበጎ ፈቃደኞች መከናወኑን አስረድተዋል፡፡ እንዲሁም ወባና መሰል በሽታዎችን የመከላከል እንዲሁም የከተሞች ጽዳትና ውበት ስራ መከናወኑን ገልጸው 450 ዩኒት ደም መለገሱንም አክለዋል። በተጨማሪም በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ወገኖች ልጆች የትምህርት ቁሳቁስ እንዲሁም ለትምህርት ቤቶች የመማሪያ ወንበርና ጠረጴዛ ድጋፍ ተደርጓል ብለዋል። በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የወተት ላሞች፣ የእንቁላል ዶሮዎች፣ በግና ፍየሎች መከፋፈላቸውን አስታውሰዋል፡፡ በቆላማ ወረዳዎች የድርቅ ተጋላጭነትን ለመከላከል በማለም ችግኞች ተተክለው እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ በዞኑ ባለፉት አራት ወራት በተከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 6 ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር የሚገመት የመንግስትና የህዝብ ሃብትን ማዳን እንደተቻለም አመልክተዋል፡፡ በዞኑ በክረምት ወራት የተካሄደው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በበጋ ወቅትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል የማድረግ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውም ተመልክቷል።
ኢኮኖሚ
በቁርጠኝነት ከተሰራ ከተማ እና ሀገርን መገንባት እንደሚቻል አዲስ አበባ ማሳያ ናት - የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት 
Nov 8, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በቁርጠኝነት ከተሰራ ከተማ እና ሀገርን መገንባት እንደሚቻል አዲስ አበባ ማሳያ ናት ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ስኬት ለሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎች አርአያ እንደሚሆንም አመራር አባላቱ ገልጸዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኮሪደር፣ የወንዝ ዳር ልማት፣ የቤት ልማት እና አቅርቦት ስራዎችን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ መስጠፌ መሀመድ፤ በጉብኝቱ አዲስ አበባ የኢትዮጵያን ገጽታ ከፍ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎችን እያካሄደች መሆኗን ተመልክተናል ብለዋል።   በተለይም የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷን የሚያጸኑ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን አይተናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በአመራሩ ቁርጠኝነት ሀገር መለወጥ የሚያስችል መልካም እድል መኖሩን ያመላከተ ነው ብለዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው፤ በኦሮሚያ ክልልም ሆነ በአዲስ አበባ ያየናቸው የልማት ውጤቶች ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና ማማ ለማድረስ በትክክለኛው መስመር ላይ መሆናችንን አመላካች ነው ብለዋል።   የኢትዮጵያን ትልሞች ከዳር በማድረስ ተጨማሪ ስኬቶችን ለማስመዝገብ ዝግጁ ነን ሲሉም ገልጸዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መነቴ ሙንዲኖ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት ለሌሎች ከተሞችም ከፍተኛ ልምድ እንደሚሆን ተናግረዋል።   ልማትን ቀጣይነት ባለው መልኩ እያረጋገጡ ለመሄድ ተግባራዊ እርምጃዎችን በላቀ ደረጃ የምንወስድበት ጊዜ ነው ብለዋል።
በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለሀብቶች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል
Nov 8, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የአገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ መኖሩን የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ በዳዳ ገለጹ። በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ውስጥ ማቲዎስ መባ ኮስሞቲክስ ማኑፋክቸሪንግ የግል ድርጅት የኮስሞቲክስ ፋብሪካ ተመርቋል።   በዚሁ ወቅት የቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ በዳዳ እንዳሉት፤ የአገር ውስጥም ሆነ የውጪ ባለሀብቶች አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶች በተሟሉበት በዞኑ በመድሃኒትና በፋርማሲዩቲካል ዘርፎች በስፋት እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል። አሁን ላይ በልዩ ኢኮኖሚክ ዞኑ ባለሀብቶች በተለያየ የማምረት ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ገልጸው፤ አሁንም ተጨማሪ ባለሃብቶች በመምጣት በሚፈልጉት ዘርፍ ተሰማርተው እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ አሁን ላይ በቋሚና በጊዜያዊነት ለ4 ሺህ 700 በላይ ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ከውጪ የሚገቡ የመድሃኒትና የፋርማሲዩቲካል ምርቶችን ለመተካት የተለያዩ ኩባንያዎች መድሃኒት እያመረቱ መሆኑን ተናግረዋል።   ማቲዎስ መባ ኮስሞቲክስ ማኑፋክቸሪንግ የግል ድርጅት ባለቤትና ስራ አስፈጻሚ አቶ ማቲዎስ መባ በበኩላቸው፤ ፋብሪካው በመጀመሪያ ዙር በ100 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክቱን ማስጀመሩን ገልጸዋል። ፋብሪካው የኮስሞቲክስ ምርቶችን በአገር ውስጥ በማምረት ከውጪ የሚገባውን ምርት ለመተካት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ ለ260 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።
በመደመር መንግሥት የሚከናወኑ የልማት ስራዎች አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክተዋል
Nov 8, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡- በመደመር መንግሥት የሚከናወኑ የልማት ስራዎች ለአካታች ኢኮኖሚ ግንባታ እውን መሆን ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም በሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በአዳማ ከተማ መሰጠቱ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ዘርፎች ላይ ያጠነጠኑ ስልጠናዎችን ወስደዋል፡፡ የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ልማት ስራዎች፣ የቤት ልማት እና አቅርቦት ስራዎችን ጎብኝተዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የስራ ሃላፊዎች እንደገለጹት ጉብኝቱ በንድፈ ሃሳብ ያገኙትን እውቀት በተግባር ለመመልከት እድል ፈጥሮላቸዋል።   የጨፌ ኦሮሚያ ምክትል አፈ ጉባኤ ኤልያስ ኡመታ በሰጡት አስተያየት አዲስ አበባ በአዲስ የልማት ስራ ተገልጣ የኢትዮጵያን እድገት በተግባር የምታሳይ ከተማ ሆናለች። ውጤቱ በመደመር መንግሥት በጋራ በመስራት የተገኘ መሆኑን ጠቅሰው፤ መንግስት ለብዝሃ የልማት አቅጣጫ የሰጠው ትኩረት ውጤት እያመጣ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን ጠቁመዋል። በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጣቸውን በተጨባጭ መመልከታቸውንም ገልጸዋል። በተለይም የከተማ አስተዳደሩ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት ያደረገው የለውጥ ስራ በእጅጉ የሚበረታታና ለክልሎች ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ እታገኝ ሃይለማርያም በበኩላቸው፤ ስልጠናው ዋና ዋና የልማት መስኮችን በመለየት ወደ ተግባር መቀየር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።   በተለይም ክልሎች ያላቸውን እምቅ ሃብት ለኢኮኖሚ ምንጭነት መጠቀም የሚችሉበትን አቅጣጫ ያመላከተ ሰለመሆኑም አንስተዋል። በተለይም በሁሉም አካባቢዎች ለቱሪዝም ልማት የሚጠቅሙ ሀብቶች እንዳሉ መገንዘብ መቻሉን ጠቅሰው፤ ይህም ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ብርሃን መሸጋገራችንን የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። በአዲስ አበባ የሚታየው ሁሉን አቀፍ ለውጥ ለሌሎች መነቃቃትን የፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል። መንግስት የግል አልሚዎችንና ማህበረሰቡን በማሳተፍ የሚያከናውነው የልማት ስራ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል።   የጋምቤላ ክልል የህብረት ስራ ማህበራት እና ማደራጃ ኤጀንሲ ሃላፊ ፓራሎክ ዋዋ ስልጠናው ለቀጣይ ስራቸው ትልቅ ግብዓት ያገኙበት መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ክልሎች ያላቸውን ሀብት ወደ ጥቅም የሚቀይሩበትን ዕድልና አማራጭ በማስፋት የአመለካከት ለውጥ ማምጣት አስችሏል ብለዋል።
የደመወዝ ማሻሻያው የሥራ ተነሳሽነታችንን ይበልጥ አጠናክሮልናል - የመንግስት ሠራተኞች 
Nov 8, 2025 64
አምቦ ፤ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡-መንግስት ያደረገው የደመወዝ ማሻሻያ የሥራ ተነሳሽነትን ይበልጥ በማጠናከር የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ እንዳበረታታቸው በአምቦ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች ተናገሩ። ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ ተቋማት የመንግስት ሠራተኞች፤ የደመወዝ ማሻሻያው የኑሮ ውድነት ጫናን በመቀነስ በቀጣይ ሕዝቡን በላቀ ቁርጠኝነትና ብቃት ለማገልገል ብርታት እንደሆናቸው ገልጸዋል። የከተማው አስተዳደር ትምህርት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ አቶ ጋዲሳ ደሳለኝ፤ በተደረገላቸው የደመወዝ ማሻሻያ ደስተኛ እንደሆኑ በመግለፅ ይህም የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እንደሚያግዝ ተግረዋል፡፡ የሥራ ተነሳሽነታቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ያበረታታቸው መሆኑንም ተናግረዋል። መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣትም ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የአምቦ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ አቶ ታደሰ ለገሰ በበኩላቸው፤ መንግስት ያደረገው የደመወዝ ማሻሻያ ተገቢ እና ወቅታዊ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል። ይህም ሕብረተሰቡን በበለጠ ፍጥነትና ጥራት በማስተናገድ የተሻለ ለውጥ ለማምጣት ተነሳሽነታቸው እንዲጨምር እንዳበረታታቸው ገልጸዋል። የደመወዝ ማሻሻያው የመንግስት ሠራተኞች የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም እንደሚያግዝ የገለጹት ደግሞ የአምቦ ከተማ ሴቶችና ህፃናት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ ወይዘሮ ትእግስት ፈይሳ ናቸው። ማሻሻያው ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቀንስ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸው፤ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ህገ ወጦች ላይ የተጠናከረ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። የአምበ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አራርሳ ከበደ፤ የመንግስት ሠራተኛ የደመወዝ ማሻሻያው በከተማ አስተዳደሩ ተግባራዊ መደረጉን አረጋግጠዋል፡፡ በዚህም ሠራተኛው ደስተኛ መሆኑን አንስተው፤ ለተገልጋዩ ሕብረተሰብ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት እርካታን ለማረጋገጥ መትጋት እንዳለበት አስገንዘበዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ማዕከል በመሆን  የሀገር ግንባታን የሚደግፉ ተግባራትን እያከናወነ ነው
Nov 8, 2025 86
ጅግጅጋ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፡-ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማሩ ባለፈ የምርምር ማዕከል በመሆን የትውልድና ሀገር ግንባታን የሚደግፉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ። በዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አብዲ አህመድ ሀሰን (ዶ/ር)፤ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የእውቀት እና የምርምር ማዕከል በመሆን ለትውልድና ሀገር ግንባታ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ተቋሙ ከመማር ማስተማሩ ባለፈ የክልሉን ብሎም የሀገርን እድገት መደገፍ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በተለይም በግብርና፣ ስነ- ህይወት፣ ምህንድስና፣ ፊዚክስ እና ሌሎችም ላይ የሚያተኩሩ ፅሁፎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ በማሳተም የእውቀትና የምርምር ማዕከል የመሆን ጥረቱን አጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል። በማሕበረሰብ አገልግሎቱ በተለይም የትምህርት፣የጤና እና የሕግ አገልግሎቶች እንዲሁም የአቅም ግንባታ ድጋፎችን በማድረግ ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አንስተው፤ ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። አሁን ላይ በጅግጅጋ እና በሼኽ ሀሰን የበሬ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ካምፓሶቹ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ እንደሚገኘ ያነሱት የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንቱ፤ ሶስተኛውን ካምፓሱን በጎዴ ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።
ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በቴክኖሎጂ ተደግፎ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ኤጀንሲው
Nov 8, 2025 81
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡- ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በአዳዲስ ቴክኖሎጂ ተደግፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ። በኤጀንሲው የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አስናቀች ሙህዬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ተቋሙ የተሟላ ሪፎርም ካደረገባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ የቴክኖሎጂ አሠራርን ማስፋት ነው። በዚህም መሠረት አገልግሎት የሚሰጠው በሲስተም መሆኑን ጠቅሰው ይህም ከማዕከል ሆኖ ወረዳ ላይ እየተሰጡ ያሉ አገልግሎቶችን ማየት የሚያስችል ነው ብለዋል። አሁን አገልግሎት እየሠጡ ካሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች የተሻለ እየበለፀገ መሆኑን ጠቁመው፤ በቅርቡ ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሠራሮች ውጤት እያስገኙ ነው ያሉት ዳይሬክተሯ፤ በቀጣይም እስከ ወረዳ ባሉ መዋቅሮች በአዳዲስ ቴክኖሎጂ የታገዙ ሥራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ከብልሹ አሠራር ጋር በተያያዘ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በ17 ባለሙያ እና አንድ ባለጉዳይ ላይ የተለያየ ርምጃ መወሰዱንና በሕግ ሂደት ላይ የሚገኝ እንዳለም ጠቅሰዋል። ከ2015 እስከ 2017 በጀት ዓመት በሐሰተኛ መረጃ ለመገልገል በሞከሩ 188 ተገልጋዮችና በአሠራር ጥሰት ደግሞ 589 ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ላይ ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል። ብልሹ አሠራርን በመከላከልና መቆጣጠር ሂደት የቴክኖሎጂ ሚና የጎላ መሆኑን ጠቁመው፤ ለአብነትም ድርጊቱ በየዓመቱ እየቀነሰ እንዲሄድ ማስቻሉን ተናግረዋል። ተገልጋዮች ትክክለኛ መረጃና ማስረጃ አቅርበው አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ አስገንዝበው፤ ሕገ ወጥ አሠራር ሲያጋጥማቸው በ7533 ነጻ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡም ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ እና ሳዑዲ አረቢያ በኢንተርፕራይዞች ልማት እና ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን አጋርነት ፈጠሩ
Nov 7, 2025 175
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ማህበር እና የሳዑዲ አረቢያ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ባለስልጣን(ሞንሻት) የስትራቴጂካዊ አጋርነት ስምምነት ተፈራርመዋል። የሳዑዲ አረቢያ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ባለስልጣን(ሞንሻት) ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ፎረም (BIBAN 2025 forum) ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል። “የዓለም የእድሎች መዳረሻ” በሪያድ እየተካሄደ የሚገኘው ፎረም ዋና መሪ ሀሳብ ነው።   በፎረሙ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ማህበር ከሳዑዲ አረቢያ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ባለስልጣን(ሞንሻት) ስትራቴጂካዊ አጋርነት መስርቷል። የአጋርነት ስምምነቱን የተፈራሙት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሳሚያ አብዱልቃድር እና የሳዑዲ አረቢያ ኢንተርፕራይዝ ባለስልጣን የአጋርነት ዘርፍ ዋና ስራ አስኪያጅ አብዱልሞህሴን ሳሌም አልሳሌም ናቸው። በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ከድር(ዶ/ር) እና የሳዑዲ አረቢያ ኢንተርፕራይዝ ባለስልጣን አስተዳዳሪ ሳሚ ኢብራሂም አልሁሴይኒ ተገኝተዋል።   አጋርነቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ ስራ ፈጣሪዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእውቀት ሽግግር እና በገበያ ተደራሽነት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ማጠናከርን ያለመ ነው። ወጣት መር፣ ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ እድገት በማረጋገጥ የቀጣናውን የጋራ ግቦች ለማሳካት እንደሚያግዝም ተመላክቷል። የሳዑዲ አረቢያ ኢንተርፕራይዝ ባለስልጣን የስራ ፈጣሪዎችን አቅም ለመገንባት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጾ ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን ለማጠናከርና ሀገሪቱ ለስራ ፈጣሪ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የገበያ እድሎችን ለመፍጠር ያላትን ራዕይ ለማሳካት እንደሚሰራ አመልክቷል። ዓለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ፎረም (BIBAN 2025 forum) ነገ ይጠናቀቃል።
የድሬዳዋ መሶብ የአንድ ማእከል እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል-ተገልጋዮች
Nov 7, 2025 117
ድሬዳዋ፣ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ)፦በድሬዳዋ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ። የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ እና የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር እና ሌሎችም አመራሮች በተገኙበት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ስራ መጀመሩ ይታወቃል። በአገልግሎቱ በመጀመሪያው ምዕራፍ አስር የተለያዩ ተቋማት 28 አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ ታግዘው እየተሰጡ ሲሆን በዚህም በርካታ ደንበኞች አገልግሎት በማግኘት ላይ ይገኛሉ። በአገልግሎት ማእከሉ የኢዜአ ሪፖርተር ተገኝቶ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች የመሶቦ አንድ ማእከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል። መሶብ ድሬ የአንድ ማዕከል ውስጥ የተገለገሉት ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በዲጂታል አሰራር በተደራጀው ማዕከል ፈጣንና ፍትሃዊ አገልግሎት ለማግኘት አስችሏቸዋል። ከተገልጋዮቹ መካከል አቶ አበበ አሰፋ እና ወይዘሮ ብርሃኔ ወልደስላሴ፤ አገልግሎቱ ገንዘብንና ጊዜን የሚቆጥብ እንዲሁም እንግልትን የሚያስቀር በመሆኑ አስደስቶናል ብለዋል። መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ከምንም በላይ ለተገልጋዮች የላቀ ትርጉም ያለው በመሆኑ በሁሉም አካባቢዎች ቢሰፋ መልካም ነው በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ሌሎች ያነጋገርናቸው ተገልጋዮች አቶ አደም አልይ እና አቶ ፈንዲሼ ታጁ፤ በተለያዩ ተቋማት በተራራቁ አካባቢዎች ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት በአንድ ስፍራ ላይ በማግኘታችን በጣም የተደሰትንበት አሰራር ነው ብለዋል። እንዲህ አይነቱ አሰራር መሰረታዊ ለውጥ የሚታይበት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል በመሆኑ ሊሰፋ ይገባል ብለዋል። የድሬዳዋ የሲቪል ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በማዕከሉ የተጨማሪ ተቋማትን አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እያደረገ መሆኑም ታውቋል።
ስፖርት
በፕሪሚየር ሊጉ ዌስትሃም ዩናይትድ እና ኤቨርተን ድል ቀንቷቸዋል 
Nov 8, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ11ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች መካሄዳቸውን ቀጥለዋል። ማምሻውን በለንደን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዌስትሃም ዩናይትድ በርንሌይን 3 ለ 2 አሸንፏል። ካሉም ዊልሰን፣ ቶማስ ሱቼክ እና ካይል ዎከርስ-ፒተርስ የማሸነፊያ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ዚያን ፍሌሚንግ እና ጆሽ ኩለን ለበርንሌይ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ዌስትሃም በሊጉ ተከታታይ ድሉን ሲያስመዘግብ በአንጻሩ በርንሌይ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል።   በሌላኛው መርሃ ግብር ኤቨርተን ፉልሃምን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢድሪሳ ጌይ እና ማይክል ኪን ግቦቹን አስቆጥረዋል። ኤቨርተን ከሁለት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል። ፉልሃም በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል። መርሃ ግብሩ ምሽትም ቀጥሎ ሲውል ሰንደርላንድ ከሊጉ መሪ አርሰናል ከምሽቱ 2 ሰዓት ከ30፣ ቼልሲ ከዎልቭስ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የደን ሀብትን የማልማትና የመጠበቅ ባህልን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ እየሰራን እንገኛለን-የደን ልማት ማህበር አባላት
Nov 8, 2025 50
ቦንጋ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የቆየውን የደን ሀብት የማልማትና የመጠበቅ ባህልን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ እየሰሩ እንደሚገኙ በካፋ ዞን የጊምቦ ወረዳ ደን ልማት ማህበር አባላት ገለፁ። የካፋ ዞን የበርካታ ተፈጥሮ ሀብቶች ባለቤት ሲሆን ከነዚህም በዓለም በቅርስነት የተመዘገበው የበርካታ ብርቅዬ ብዝሃ-ህይወት መገኛው የካፋ ባዮስፌር አንዱ ነው። የካፋ ባዮስፌር በውስጡ ጥብቅ ደኖችንና ዘላቂ የልማት ሞዴልን የያዘ ሲሆን የአረቢካ ቡና፣ የበርካታ ሀገር በቀል ዛፎች፣ የመድኃኒት እፅዋት፣ የብርቅዬ እንስሳትና አእዋፋት ዝርያዎች መገኛ ነው።   በዚህ ባዮስፌር ውስጥም አሳታፊ የደን ልማት ማህበራት የሚገኙ ሲሆን ማህበራቱም በዞኑ የደን ሀብትን የማልማትና የመጠበቅ ባህልን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ እየሰሩ መሆናቸውን ይገልፃሉ። በጊምቦ ወረዳ ሚቺቲ ቀበሌ ውስጥ ከሚገኙ የደን ማህበራት መካከል የበካ ደን ልማት ማህበር ሰብሳቢ አቶ መብራቱ ገብረመስቀል ከአያቶቻቸው የተረከቡትን ደን የመጠበቅ ባህልን ማስቀጠላቸውን ጠቅሰው ማህበራቸው 130 አባላትን ይዞ ከ600 ሄክታር በላይ መሬት የሸፈነውን ስፍራ እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።   ከጥበቃው ጎን ለጎንም በክፍት ቦታዎች ላይ አዳዲስ ችግኞችን በመትከል የአካባቢው ስነ ምህዳር እንደተጠበቀ እንዲቆይ እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል። በአካባቢው ዘመናዊ የደን አጠባበቅ ስርዓት እንዲኖር ተደራጅቶ መንቀሳቀሱ ዘላቂ ልማትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የማህበሩ አባል አቶ ገረመው አሰፋ ናቸው።   ማህበሩ በስሩ ባሉት ስድስት ሳይቶች የተለያዩ ኮሚቴዎችን በማዋቀርና የችግኝ ጣቢያዎችን በማቋቋም በየዓመቱ ተጨማሪ ችግኞችን በመትከል የደን መጠኑ እንዲጨምር እያደረገ መሆኑንም ገልፀዋል። የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት መምሪያ የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታሪኩ ወልደሚካኤል፣ የካፋ ማህበረሰብ በደን አጠባበቅ ላይ የቆየ ልምድ አለው ብለዋል።   ዘመናትን የተሻገረው የካፋ ማህበረሰብ የደን አጠባበቅ ባህል አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰው ይህም በርካታ ትሩፋቶችን እያስገኘ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በዚህም በዞኑ 66 ሺህ 500 ወንድና ሴት አባላት ያላቸው 265 ማህበራት ተደራጅተው ከ218 ሺህ 195 በላይ ሄክታር ደን በመጠበቅ ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል። የካፋ ባዮስፌር የአረቢካ ቡና መገኛ ብቻም ሳይሆን ከአምስት ሺህ በላይ የቡና ዘረመሎች፣ ሀገር በቀል የዛፍ ዝርያዎች እንዲሁም የተለያዩ አእዋፋት፤ ብርቅዬ የአንበሳ ዝርያና ሌሎች እንደሚገኙበትም ገልፀዋል። በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው የካፋ ባዮስፌር 760 ሺህ ሄክታር መሬትን የሚሸፍን ሲሆን ከዚህም ውስጥ 52 በመቶው ጥብቅ ደን መሆኑን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
በጋምቤላ ክልል በባዮስፌር ሪዘርቭ የተመዘገቡ ደኖችን ለዘላቂ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ለማዋል ትኩረት ተደርጓል
Nov 8, 2025 61
ጋምቤላ፤ጥቅምት 29/ 2018 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በባዮስፌር ሪዘርቭ የተመዘገቡ ደኖችን ለዘላቂ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ለማዋል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በበኩሉ በክልሉ በባዮስፌር ሪዘርቭ የተመዘገቡ የተፈጥሮ ደን ሀብቶችን በመጠበቅ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውን ለማጉላት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሯች ባየክ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከልና ብዝሃ ህይወት መጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።   የጋምቤላ ክልልም ባከናወናቸው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች የማጃንግና የአኝዋሃ ዞኖች የተፈጥሮ ደኖች በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት /ዩኔስኮ/ በባዮስፌር ሪዘርቭ መመዝገባቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል። በክልሉ በባዮስፌር ሪዘርቭ የተመዘገቡ ደኖች በውስጣቸው በርካታ የእንስሳት፣ የዕጽዋትና የውሃ አካላትን የያዙ መሆናቸውን ጠቁመዋል። እነዚህ ሀብቶችን በመጠበቅና በመንከባከብ ለዘላቂ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። በዩኔስኮ በባዮስፌር ሪዘርቭ የተመዘገቡት የተፈጥሮ ደኖች የአየር ንብረት ሚዛንን በማስጠበቅ ለዘላቂ የግብርና ልማት የጎላ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል። የተፈጥሮ ደን ሀብቶቹ ብዝሃ ህይወትን መያዛቸው በዘርፉ ለሚደረጉ ጥናትና ምርምር ስራዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥሩም ገልጸዋል። የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኮንግ ኛክ በበኩላቸው፥ እንደ ሀገር በዩኔስኮ እውቅና አግኝተው በባዮስፌር ሪዘርቭ ከተመዘገቡት ስድስት የተፈጥሮ ደኖች መካከል ሁለቱ በጋምቤላ ክልል እንደሚገኙ ተናግረዋል።   በመሆኑም የተፈጥሮ ደኖች በዓለም አቀፍ ደረጃ በባዮስፌር ሪዘርቭነት ያገኙትን እውቅናና በውስጣቸው የሚገኙ የብዝሃ ህይወት ሃብቶችን በማስተዋወቅ ለቱሪዝም ልማት ለማዋል እየተየሰራ ነው ብለዋል። ቢሮው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በደን ሀብቶች ላይ ተጨማሪ የጥናት ስራዎችን በመስራት የዘርፉን ጥቅም የማሳደግና የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት ስራ እንደሚከናወንም አመልክተዋል።
የአፍሪካ ጥያቄ ምጽዋት አይደለም የምንፈልገው የአየር ንብረት ፍትህ እና ፍትሃዊ የፋይናንስ አቅርቦት ነው - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Nov 8, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ምጽዋት አትፈልግም ጥያቄያችን የአየር ንብረት ፍትህ እና ፍትሃዊ የፋይናንስ አቅርቦት ሊኖር ይገባል የሚል ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ለአየር ንብረት ለውጥ ዝቅተኛ ድርሻ ያላቸው የአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛውን የጉዳት ቀንበር ሊሸከሙ አይገባምም ብለዋል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) ከህዳር 1 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በብራዚል ቤለም ይካሄዳል። “የአየር ንብረት እርምጃ እና ትግበራ” የጉባኤው ዋና መሪ ሀሳብ ነው። ከዋናው ጉባኤ በፊት የቤለም የአየር ንብረት የመሪዎች ጉባኤ ተካሂዷል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር አፍሪካ ወደ ኮፕ 30 ጉባኤ በጠንካራ አቋም መምጣቷን ገልጸው አህጉሪቷ የለውጥ ወኪል ናት ሲሉ ተናግረዋል። ከፀሐይ ኃይል ማመንጫ ስፍራዎች እስከ አረንጓዴ ኢንቬሽን ባለቤት ወጣቶች የያዘችው አፍሪካ ቀጣዩ ጊዜ ፍትሃዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ዝቅተኛ የካርቦን ልህቀት እንዲሆን የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ ገልጸዋል። አፍሪካ የዓለም 40 በመቶ የታዳሽ ኃይል አቅም ያላት ቢሆንም የምታገኘው የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ ከ12 በመቶ በታች መሆኑን አመልክተዋል። እኛ የጠየቅነው በጎ አድራጎት አይደለም ያሉት ሊቀ መንበሩ የምንፈልገው የአየር ንብረት ፍትህ፣ ፍትሃዊ የፋይናንስ፣ ቴክኖሎጂ እና እድሎች ተደራሽነት ነው ብለዋል። ለአየር ንብረት ለውጥ ውስጥ ዝቅተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ሀገራት ከፍተኛውን ቀንበር መሸከም የለባቸውም ነው ያሉት። ኮፕ 30 ዓለም ከቃል መግባት ወደ ለውጥ፣ ከተጋላጭነት ወደ ጥንካሬ መሸጋገር እንዳለበት ገልጸው የአየር ንብረት ለውጥን የመከላከል ስራ በአጋርነት፣ በፍትሃዊነት እና የጋራ ብልጽግና እሳቤዎች ሊመራ እንደሚገባውም አመልክተዋል። ግማሽ መፍትሄ ብቻ የሚያመጡ እርምጃዎችን የመውሰድ ጊዜ አብቅቷል፤ አሁን የሚያስፈልገው ድፍረት የሞላበት እና የጋራ የተግባር ምላሽ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በበጋ ወራት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ለማከናወን ዝግጅት ተደርጓል
Nov 7, 2025 111
ጎንደር፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በዘንድሮ የበጋ ወራት በ879 ነባርና አዲዲስ ተፋሰሶች ላይ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የተፈጥሮ ሀብት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል፡፡   የመምሪያው ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ እንደገለጹት፤ ባላፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና የልማት ሥራዎች የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት በማሳደግ ተጨባጭ ለውጥ አምጥተዋል፡፡ ባገገሙ ተፋሰሶች ላይ አርሶ አደሩን በንብ ማነብ፣ በእንስሳት ማድለብ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማትና በሌሎች የልማት ሥራዎች በማሳተፍ የተሻለ ገቢ እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡ በቅድመ ዝግጅት ወቅት በዞኑ በተለያዩ ወረዳዎች ከ473 ሺህ በላይ ተሳታፊ አርሶ አደሮችን በ3ሺህ 66 የልማት ቡድኖች የማደራጀት ሥራ መከናወኑንም አስረድተዋል፡፡ ከ41ሺህ ሄክታር በላይ የተራቆቱ መሬቶች ላይ የእርከንና ክትር ሥራዎችን ጨምሮ የውሃ ስርገትን የሚጨምሩ የልማት ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ የሚከናወንባቸውን ተፋሰሶች በመጪው የክረምት ወራት በስነ ህይወታዊ ዘዴ ለማጠናከርም ከ141 ሚሊዮን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች የማፍላት ሥራ ይከናወናል ብለዋል፡፡   ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወነው የችግኝ ተከላና ክብካቤ ሥራ የዞኑን የደን ሽፋን በአሁኑ ወቅት 14 ነጥብ 5 በመቶ ለማድረስ መቻሉን አስረድተዋል፡፡ የዞኑ አርሶ አደሮች በለሙ አካባቢዎች ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በማግኘታቸው ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ልዩ ትኩረት እየሰጡ መጥተዋል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ክንዱ ዘውዱ ናቸው፡፡   በዞኑ የተቋቋሙ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ጽህፈት ቤቶች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥና ያገገሙ ተፋሰሶች ዘላቂነታቸው እንዲጠበቅ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። የላይ አርማጭሆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስረሳው ደሴ በበኩላቸው እንዳሉት ወረዳቸው በተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ ሞዴል ከሚባሉ ወረዳዎች የሚጠቀስ ነው። አርሶ አደሮችም በለሙ ተፋሰሶች ላይ በንብ ማነብና በፍራፍሬ ልማት በመሰማራት የተሻለ ገቢ በማግኘት ኑሮዋቸውን እየለወጡ መምጣታቸውን አስረድተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 202
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 418
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል።   ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል።   ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 337
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው  
Oct 24, 2025 607
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡   በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡   ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡   በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ሐተታዎች
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 153
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 393
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
የብዙዎች ቤት…
Oct 27, 2025 535
እስካሁን በተደረገ የጥናት ውጤት መሠረት ከ81 በላይ የአጥቢ እንስሣት፣ ከ450 በላይ የአዕዋፍ እና ከ400 በላይ የእፅዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው። ከእነዚህ መካከል አምስቱ የአዕዋፍ ዝርያዎች በዚህ ሥፍራ ብቻ ይገኛሉ፤ ከአምስቱ መካከል በተለይም የአንዷ ዝርያ ዓለም አቀፍ የዘርፉ ተመራማሪዎችንና ጎብኚዎች ቀልብ መሳቡ ይጠቀሳል። ከአካባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ጋር መጣጣም የቻሉ የቆላ እፅዋት (ዛፎች) በምቾት በስፋት እንደሚገኙበትም ይገለጻል። የተመሠረተው በ1958 ዓ.ም ሲሆን፤ ስፉቱም 591 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው፤ በቁጥርም ሆነ በሥብጥር የብዙዎች መኖሪያ የሆነው ይህ ሥፍራ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ይሰኛል። መንግሥት በሰጠው ትኩረት ከነበረው በተሻለ ሁኔታ እንስሣቱም ሆኑ እፅዋቱ እየኖሩ ነው፤ ከሕገ ወጥ ድርጊትም እንዲጠበቁ ማድረግ መቻሉን የፓርኩ ኃላፊ አደም መሐመድ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በፓርኩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁንም ለ247 ወገኖች ቋሚ እና ለ2 ሺህ 535 ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ዓመትም በ1 ሺህ 751 የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንደተጎበኘ ኃላፊው ገልጸዋል።
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 905
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል።   ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው።   የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።   እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።   “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው።   ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል።   ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።   የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1864
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2197
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3063
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3161
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 1144
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 777
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6615
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5088
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 56172
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51641
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32348
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 29860
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26163
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 24777
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24472
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24392
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 56172
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51641
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32348
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 29860
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
​​​​​​​ባሕር በር -የታሪክና የእድገት ስብራት ወጌሻ 
Nov 5, 2025 341
ባሕር በር የታሪክ እና የእድገት ስብራት ወጌሻ በቀደሰ ተክሌ የምሥራቅ አፍሪካዋ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ስሟ ገኖ እንዲነሳ ካደረጓት መካከል የሰው ዘር መገኛነት፣ የራሷ የሆነ የአስተዳደር ሥርዓት፣ የዘመን አቆጣጠር፣ ቋንቋና ፊደል ያላት ሉዓላዊት ሀገር መሆኗ ተጠቃሽ ነው ። የገናና የጥበብ ባለቤት መሆኗን አክሱም እና ላሊበላ ዛሬም ቆመው ይመሰክሩላታል። በጥንት ጊዜ ወደብ የስልጣኔ ተጽዕኖ ፈጣሪነት መገለጫ በነበረበት ጊዜ ኢትዮጵያም ስሟ ጎልቶ ይነሳ ነበር። ወደብ ዓለምን እርስ በእርስ ከማስተሳሰር ባለፈ የግብይት የጀርባ አጥንት ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል፤ ዛሬም እያገለገለ ይገኛል። ሀገራት አዋጭ የንግድ ስትራቴጂ ቀይሰው የተለያዩ ወደቦችን የመጠቀም ልምዳቸው በታሪክ ውስጥ ጎልቶ የሚነሳ ነው። የንግድ ሥርዓታቸውን በወደብና በየብስ ከሚያከናውኑ የዓለም ሀገራት መካከል ደግሞ ኢትዮጵያ አንዷ ናት። የታሪክ ድርሳናት እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘመነ መንግስታት የተለያዩ ወደቦችን በባለቤትነት አስተዳድራለች። ከአክሱም ዘመነ መንግሥት ጀምሮ እስከ ደርግ መንግስት ድረስ አዱሊስ፣ አሰብ፣ ዘይላ፣ ምጽዋና ሌሎች ወደቦችን ለኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ትገለገል ነበር። ይሕ የኢትዮጵያ የወደብ ባለቤትነት ታሪክ እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ የዘለቀ እንደነበር በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሰቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምሕርት ክፍል መምሕር አጥናፉ ምትኩ ይናገራሉ። ወደብ ከኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳው ከፍተኛ እንደሆነም አውስተዋል።   በታሪክ ኩነት ውስጥ የተፈጠረ ሴራና ተንኮል ኢትዮጵያ የባሕር በር አልባ ሀገር እንድትሆን አድርጓታል። ይሕም ከሆነ ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ ተቆጥሯል። በዚሕም ኢትዮጵያ ለወደብ ኪራይ በየዓመቱ ብዙ ቢሊዮን ብር እየከፈለች የወጪ እና ገቢ ንግድን የማንቀሳቀስ እዳ ተጭኖባታል። ይሕም የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ወደ ኋላ ከሚጎትቱ ጉዳዮች አንዱ ሆኖ ዛሬ ድረስ ዘልቋል። የወደብ አገልግሎት ነጻነት ማጣት፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ዋጋ መጨመር፣ ማዳበሪያን ጨምሮ አስፈላጊ ግብአቶች መዘግየትና በወቅቱ አለመድረስ፣ በዚሕም የሰብል ልማት ስራዎች ላይ ችግሮች መስተዋል ከባሕር በር ባለቤትነት እጦት ጋር የመያያዝ እድላቸው ሰፊ ነው። እነዚሕ ችግሮች ደግሞ ተደማምረው ለኑሮ ውድነት መፈጠር አስተዋጾኦ ይኖራቸዋል ማለት ይቻላል። በታሪክ አጋጣሚ የተፈጠረው ስብራት እያስከተለ ያለው ጉዳት አሁን ላይ ለኢትዮጵያ የሕልውና ጉዳይ በመሆኑ በታሪካዊ ዳራ መሠረት መጠገን ያስፈልጋል። ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ከ130 ሚሊዮን ያሻቀበ የሕዝብ ቁጥር፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና ሀገራዊ የቆዳ ስፋት ገፊ ምክንያቶች ከሚባሉት ውስጥ ይጠቀሳሉ። በሌላ በኩል ከዚሕ ቀደም የነበረው የሀገሪቱ ባሕር በር ባለቤትነት ማስረጃ ዛሬ ላይ አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። መንግሥት የጀመረው የባሕር በር ባለቤት የመሆን ጥያቄ በመሬት ተዘግቶ የመኖር ታሪክ እንዲያበቃ የሚያደርግና በዓለም አቀፍ ሕግ ተፈጥሮን በጋራ ተጠቅሞ የመልማት መብትን የሚያስጠብቅ መሆኑ እውን ነው። ለሦስት አስርት ዓመታት ታፍኖ የቆየው የቀይ ባሕር ባለቤትነት ጥያቄ የመንግስት ቁርጠኝነት እንዳለ ሆኖ ዜጎችም አጥብቀው በመያዝ መልስ እስኪያገኝ ድረስ መስራት ይጠበቃል። የሀገርና የሕዝብ የዘመናት ጥያቄ የሆነው የባሕር በር እስኪሳካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ከሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሚጠበቅ መምሕር አጥናፉ ይገልጻሉ። ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት መሆን የታሪኳና ዕድገቷ ወጌሻ ነው ያሉት መምሕር አጥናፉ ኢትዮጵያ የባሕር በር ለመጠቀም የሚያስችላት ታሪካዊ መብት አላት። ይሕን ታሪካዊ መብቷን የምታረጋግጥበት ትልቁ መሣሪያ ደግሞ ያላት ጠንካራ የዲፕሎማቲክ አቅሟ ነው። ከዓለም ሀገራት ጋር ያላት መልካም ግንኙነት ተናግሮ ለማሳመን እውነታን ለመግለጽ የሚያስችላት ነው። ይሕንንም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በዓለም ፊት አረጋግጣለች። ይሕን የሕዳሴ ድል በቀይ ባሕር ላይ የማትደግምበት ምንም ምክንያት አይኖርም። በተለይ ኢትዮጵያ ያላት የጋራ ተጠቃሚነት መርሕ በዓለም ላይ ተቀባይነት ያለውን ሀሳብ ይዛ እንድትቀርብ እያስቻላት ይገኛል። ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የሚሰጠው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲዋ ተፈጥሮን ተባብሮ በማልማት እንጠቀም የሚል መሠረት ያለው ነው። መምሕር ይስሐቅ ንጉሤ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሰቲ የምጣኔ ሀብት መምሕር ሲሆኑ የባሕር በር ጉዳይ የኢኮኖሚ ዕድገት ማጠንጠኛ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣቷ በፈጣን ዕድገቷ ላይ መሰናክል ሆኖ መዝለቁን ተናግረዋል።   በተለይ የዓለም ሀገራት ከፍተኛው የንግድ፣ የኢኮኖሚና ሀብት እንቅስቃሴ የሚታይበት እና የሀገራት የንግድ ልውውጥ የሚካሄድበት የቀይ ባሕር ቀጠና ላይ ያለውን አብሮ የመስራትና ከማደግ ዕድል ኢትዮጵያ ያለአግባብ መገለሏን ያነሳሉ።ይሕም በሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትና በሌሎች ላይ ያሳደረው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ እንደሆነ ነው ያገለጹት። የባሕር በር ጥያቄ የምጣኔ ሀብት ዕድገትን በማሳለጥ ሀገሪቱ ከልመና ለመውጣት ያላትን ዕድል እንድትወስን ያስችላታል የሚሉት መምሕሩ ፤ለስኬቱም የተጀመረውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማጠናከር እንደሚገባም ነው የገለጹት። እንደ መምሕሩ ገለጻ ከዓለም አቀፍ መርሆችና ስምምነቶች እንዲሁም ካለን መልከአ ምድራዊ አቀማመጥና ታሪክ አንጻር ለኢትዮጵያ የባሕር በር ተገቢ ነው። ይሕ እንዲሳካም መንግስት ካሳየው ቁርጠኝነት በተጨማሪ ሁሉም በተቀናጀ መንገድ የሚያደርገውን ጥረት ማጠናከር ይኖርበታል። መንግስት የዘመናት የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ የቆየውን የባሕር በር ጉዳይ በግልጽና በይፋ መረጃ በመስጠት ዓለም አቀፍ አጀንዳ እንዲሆንም ጭምር እያደረገ ያለውን ጥረትንም አድንቀዋል። ታሪክ በኩነቶች መካከል መጥፎም መልካም ሆኖ ያልፋል። በታሪክ የባሕር በር ባለቤትነታችን የገጠመውን ስብራት ለመጠገን የሚያስችል ወጌሻ ያስፈልጋል። በታሪክ ሂደት መልካሙ ወደ መጥፎ ሁኔታ እንደሚቀየር ሁሉ የተበላሸን ወደ መልካም የመቀየር ዕጣ ፈንታ ያለው የዛሬው ትውልድ ላይ ነው። ለእዚሕ ደግሞ ትውልዱ በሕዳሴው ግድብ ከመንግስት ጎን ሆኖ ያሳየውን አንድነትና ሕብረት በባሕር በርም መድገም አለበት። ታሪካዊ ዳራን፣ ዲፕሎማሲን፣ ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታና ሕግን ተከትሎ በአብሮነት ከተሰራ ያኔ የተበላሸው ይቃናል፤ ያጣነውን እናገኛለን። "እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል" ዓይነት እንስሳዊ ግብር በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሊሰማ አይገባም፤ መሰማትም አይኖርበትም። ኢትዮጵያ ብታደግ ለቀጣናው ኩራት፤ ለአፍሪካም ልዕልና እንጂ ጥፋት የሚያስከትል እንዳልሆነ መገንዘብና የትብብር ልማትና ዕድገትን ባሕል ማድረግ ሊለመድ ይገባል። ሰላም!
የዳሰነቾች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ''
Oct 30, 2025 933
የዳሰነች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ'' (በጣፋጩ ሰለሞን ከጂንካ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ዳሰነቾች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በአብሮነት ተጎዳኝተው ይኖራሉ። የብሔረሰቡ አባላት ዋነኛ መተዳደሪያ ከብት እርባታ ሲሆን፤ ከከብት እርባታው ጐን ለጐን በዝቅተኛ ደረጃ በግብርናና በዓሳ ማስገር ስራ ይተዳደራሉ፡፡ ዳሰነቾች በሰሜን ከሐመር፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ በምስራቅ ከቦረና በስተ ምዕራብ ደግሞ ከኛንጋቶም ማህበረሰብ ተጎራብተው ይኖራሉ። ዳሰነቾች ከኩሽቲክ የቋንቋ ነገድ የሚመዘዝ ''አፍ ዳሰነች'' የተሰኘ የመግባቢያ ቋንቋም አላቸው። ዳሰነቾች የተለየ የአለባበስ፣ የአጋጌጥ፣ የቤት አሰራር እና የባህላዊ የሙዚቃ ስልተ ምትን ጨምሮ አስደማሚ ባህሎች እና ማራኪ የመልክዓ ምድር አቀማመጥን የታደሉ ናቸው። ዳሰነቾች ከሚታወቁባቸው አስደማሚ ባህሎች ውስጥ አንዱ የሆነው አለመግባባቶችን በውይይት የሚፈቱበት የ''ጀለባ''ስርዓት ተጠቃሽ ነው። ይህ ስርዓት ግጭቱ ቂምና ቁርሾ በማይሻገርበት መልኩ በዘላቂነት የማስወገድ አቅም ያለው ሲሆን የማይናወጥ ሰላምና ወንድማዊ ትስስር እንዲጠናከርም ሚናው የጎላ ነው። ዕሴቱ የዳሰነቾች የአኗኗር ቁመና የሚለካበትና የሚመዘንበት መጻኢንም የሚተለምበትም ጭምር ነው። ስለሆነም በዳሰነቾች ዘንድ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል ነው የሚባለው። የባህሉ ተመራማሪ ሊዮን አርሎት 'ጀለባ'' የተሰኘው ባህላዊ ዳኝነት ከአካባቢው ሰላም አልፎ ለቀጠናው ወንድማማችነት መጠናከር ትልቅ ሚና ያለው የፍትህ ስርዓት መሆኑን ያነሳሉ። በ''በጀለባ'' ስርዓት ባህላዊ የዳኝነት አሰጣጥ እርከኖች እንዳሉ ጠቅሰው፥ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ''ኖሞ'' የተሰኙ ሽማግሌዎች ወደ ስፍራው በማቅናት የግጭቱን መንስኤ በማጣራት ''ቶሎል'' ለተሰኙ ሌሎች ሽማግሌዎች የሚያሳውቁበት አሰራርም አላቸው። እንደ ግጭቱ ቅለትና ክብደት ''ቶሎል'' በተሰኙ ሽማግሌዎች ተለይቶ ቀለል ያለው ''ካባና'' በተሰኙ ዳኞች ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን፥ ጉዳዩ ከበድ ያለ ከሆነ ደግሞ የመጨረሻው ውሳኔ ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች ይሰጣል። ከነፍስ ማጥፋት በስተቀር ሁሉም ውሳኔዎች ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች እልባት ያገኛሉ። የነፍስ ማጥፋት ወንጀል ሲከሰት ግን ጉዳዩን ለመንግሥት አሳልፎ በመስጠት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ ይደረጋል ። ነፍስ ያጠፋው ሰው የእርምት ጊዜውን አጠናቆ ማህበረሰቡን ለመቀላቀል ሲወስን ባህላዊ የዕርቅ ስነ-ስርዓት ተዘጋጅቶ በዳይና ተበዳይ ይቅር የሚባባሉበትም ስርዓት እንዳለ የባህሉ ተመራማሪ ይናገራሉ።   በዳሰነቾች ባህል ልዩነቶች ሰላማዊ በሆነ መንገድ በዘላቂነት መንገድ የመፍታት ዘመናትን የተሻገረ ድንቅ ዕሴት መኖሩን የሚያነሱት የብሔረሰቡ አባል አሸቴ ነካሲያ፤ “በዳሰነች ብሔረሰብ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል'' ይላሉ። በዳሰነቾች አለመግባባቶች በውይይት የሚፈቱበት ስርዓት እንዳለ ጠቅሰው፥ ''ናብ'' በተሰኘው የዳኝነት ስፍራ አለመግባባቶች ውለው ሳያድሩ እልባት ያገኛሉ ብለዋል። ሌላው የብሔረሰቡ አባል ሎቶያቡስ ሎኪሰሬሬ በበኩላቸው የባህል መሪዎች የተጣላን ማስታረቅ፣ ትውልዱን የመግራትና በስነ-ምግባር የማነፅ ኃላፊነት እንዳላቸው ጠቅሰዋል። ''ማንም ሰው ከባህል መሪዎች ትዕዛዝ አያፈነግጥም'' የሚሉት አቶ ሎቶያቡስ፥ ሁሉም እርስ በእርስ በመከባበር እና ችግሮች ሲኖሩ በውይይት በመፍታት አብሮነቱን ያጠናክራል ብለዋል።   ወጣቱ ለባህል መሪዎች ታዛዥ ነው የሚሉት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ የብሔረሰቡ አባል ሎሲያ ሎብቻ ወጣቶች ለአካባቢው ሰላም ዘብ እንዲቆሙ፣ ከአጎራባች ህዝቦች ጋር በፍቅር እንዲኖሩ በማስተማር ወጣቱን በስነ-ምግባር የማነፅ ስራ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። የዳሰነች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ በበኩላቸው የዳሰነች ህዝብ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ከወረዳው አልፎ ለቀጠናው ሰላም ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የብሔረሰቡ ባህላዊ የሽምግልና ስርዓት ትውልዱን በመግራት በስነ- ምግባር የታነፀ ዜጋ እንዲፈጠር እንዳደረገም አስረድተዋል።   የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የሶሻል አንትሮፖሎጂ መምህርና ተመራማሪ አጎናፍር ሰለሞን፤ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓቶች ለዘመናዊው የፍትህ ስርዓት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ብለዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች ቅጣት በመጣል ጥፋተኝነት እንዲሰማ የሚያደርጉ ሳይሆኑ፤ እውነተኛ ይቅርታን የሚያሰፍኑና ለአብሮነት የሚበጁ ዕንቁ ባህሎች እንደሆኑም አብራርተዋል።   ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹ በግለሰብ ተጠቃሚነት ላይ ሳይሆን በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት የሚያደርጉ በመሆናቸው ከዘመናዊው የፍትህ ስርዓት በይበልጥ ለአብሮነት መጠናከር አስተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹም ለሀገራዊ መግባባት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ፥ እሴቶቹ ተጠብቀው፣ ለምተውና ጎልብተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት እንደሚገባም መክረዋል። ሀገራችን ቂምና ቁርሾን የወለዱ ያለመግባባቶች በዘላቂነት በሰለጠነና ሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ሁሉንም ያሳተፈ ስራ እየሰራች እንደሆነ ያነሱት መምህርና ተመራማሪው አጎናፍር ሰለሞን ዕሴቶቹ በማህበረሰቡ ዘንድ ካላቸው ተቀባይነት እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን ከማገዝ አንጻር ጉልህ ሚና ስለሚኖራቸው መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም