ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበትን ሥርዓት እየገነባ  ይገኛል
Dec 30, 2025 48
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበትን ስርዓት እየገነባ ይገኛል ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። በባሕርዳር ከተማ 123 ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ብር በሆነ ወጪ የተገነባ የሴቶችና ህፃናት ማገገሚያ ማዕከል ዛሬ ተመርቋል። ማዕከሉን የክልሉ የጤና ፣ የሴቶች፤ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች በጋር በመተባበር እንዳስገነቡት ተገልጿል።   በምረቃው ሥነ- ሥርዓት ላይ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበት ሥርዓት እየገነባ ይገኛል። ‎በባሕርዳር ከተማ የተገነባው የማገገሚያ ማዕከልም የመደመር መንግስት በተለይ ለተጋላጭ የሕብረተሰብ ክፍሎች የሰጠው ትኩረት አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። ‎በተቋማት ትብብር በአጭር ጊዜ የተገነባው ማገገሚያ ማዕከሉ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶችና ህፃናትን ፈጥኖ በማስገባት ወደ ቀደመ ሕይወታቸው እንዲመለሱ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ‎ሚኒስቴሩ ማዕከሉ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ በቀሳቁስና ሌሎች የድጋፍ ዓይነቶች አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። ‎‎በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶችና ህፃናት እንዳያገግሙ በመደገፍ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ‎በቀጣይም ተመሳሳይ ማዕከላትን ወደ ሌሎች ከተሞች የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። ‎የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ ፤ የማዕከሉ መገንባት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።   ‎ማዕከሉ ‎በሶስት ሺህ 200 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ በሶስት ወራት ውስጥ የተገነባ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ ናቸው። በውስጡ የመኝታ፣ የሕክምና፣ የስልጠና፣ የአስተዳደርና ሌሎች አገልግሎቶች የሚሰጡ 35 ክፍሎችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል። በ‎‎ተመሳሳይም በጎንደር ከተማ መሰል ማእከል እየተገነባ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በደሴና በሌሎች ከተሞች በቀጣይ ተደራሽ ለማድረግ ቢሮው ከክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮና የከተማ አስተዳደሮች ጋር እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ‎የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)‎ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በባሕርዳር ፈለገ ሕይወት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግቢ የተቋቋመውን ሁለንተናዊ የለውጥ መሪነት ስርዓተ ፆታ እኩልነት የስልጠና ማዕከልንም ጎብኝተዋል።
ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት በተጓዳኝ ሰላምን ለማፅናት ድጋፋችንን እናጠናክራለን- አሽከርካሪዎች 
Dec 30, 2025 34
ደብረብርሃን፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት ጎን ለጎን ሰላምን ለማፅናት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የደብረ ብርሃን ከተማ የታክሲ አሽከርካሪዎች ገለጹ። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ከታክሲ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ጋር በሰላም ማስከበር ላይ ዛሬ ተወያይቷልⵆ ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ዓለሙ አሽኔ፤ በትራንስፖርት ዘርፉ ቀልጣፋ አገልግሎት ለሕብረተሰቡ ከመስጠት በተጓዳኝ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የበኩላቸውን ሲወጡ እንደቆዩ ተናግረዋል።   ይህንን በማጠናከር ከፖሊስ ጋራ በመተባበር ወንጀልን ለመከላከል በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ሸዋለም ግዛቸው በበኩላቸው፤ የከተማዋ እድገት እንዲፋጠን የትራንስፖርቱ ዘርፍ ያለውን ድርሻ ለማሳካት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። መንግስት የሚያወጣውን ደንብና መመሪያ አክብረው በመስራት በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በዘላቂነት ለማፅናት በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ በንቃት በመሳተፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል።   የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳንኤል እሸቴ በበኩላቸው፤ ከከተማው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር በተከናወነው ሕግ የማስከበር ስራ ሰላምን ማስጠበቅ መቻሉን ተናግረዋል። ሰላምን አስጠብቆ በማዝለቅ የከተማዋን ልማት ለማፋጠን እየተከናወነ ባለው ስራ ውስጥ የታክሲ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች የድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም የታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ሕገወጥነትን በመከላከል ፈጣንና ውጤታማ አገልግሎት ለሕብረተሰቡ እንዲሰጡ ለማስገንዘብ ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል።   የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ደጀኔ ልመንህ፤ የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማፅናት የነዋሪዎች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋልⵆ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች በሰላም ማስጠብቅና በወንጀል መከላከል የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ለሕብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በውይይቱ ላይ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖችን ጨምሮ ሌሎችም አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በከተማዋ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ ነው
Dec 30, 2025 89
አዳማ ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ መሆናቸውን የከተማዋ አስተዳደር ገለጸ። የዘንድሮውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ሸማቾችንና አምራቾችን ለማገናኘት ያለመ የንግድ ትርዒትና ባዛር በአዳማ ተከፍቷል። የአዳማ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ማቲያስ ሰቦቃ በወቅቱ እንደገለፁት፤ በከተማዋ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ ነው።   ለዚህም የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የግብርናና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶች የዋጋ ንረትና ገበያ ማረጋጋት ላይ አበረታች ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በተለይ ወተት፣ እንቁላል፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የምግብ ዘይትና ሌሎች የፍጆታ እቃዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የንግድ ትርዒትና ባዛሩ ሸማቹን ከአምራቹ ጋር በቀጥታ በማገናኘት በበዓል ምክንያት የግብርና ምርቶችና ሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ እንዳይኖርና ገበያን ለማረጋጋት በማለም የተዘጋጀ መሆኑን አመልክተዋል። በመክፈቻው ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የአዳማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አሸናፊ አጀማ በበኩላቸው፤ በከተማዋ የኑሮ ውድነትን ለመግታት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።   በዚህም አምራቹ በቀጥታ ምርቱን ለሸማቹ እንዲያቀርብ በማድረግ የዋጋ ንረትን በመቀነስ ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እንዲፈፅም እየተደረገ መሆኑን አክለዋል። የከተማ አስተዳደሩ የግብርና ምርቶች የመሸጫ ማዕከላት በመገንባት የተለያዩ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለገበያ እያቀረበ መሆኑን ገልጸው በዚህም ስንዴ፣ ጤፍ፣ ዱቄት፣ የወተት ተዋፅኦን ጨምሮ ዶሮና እንቁላል እንዲሁም ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል ብለዋል። የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስራ አስፈፃሚ አቶ ብዙነህ ግርማ በበኩላቸው፤ኢንቨስትመንት ግሩፑ ገበያን በማረጋጋት ረገድ በቀን ሁለት ሺህ 500 ሊትር ወተትና እንቁላል ለገበያ እያቀረበ መሆኑን ጠቁመዋል።   በተጨማሪም ግሩፑ የገበያ ትስስር በመፍጠር የግብርና ምርቶችና ሸቀጦች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች እንዲደርስ እያደረገ መሆኑን ጠቅሶ ከከተማዋ የንግድ ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ባዛር ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል-ኮሚሽኑ
Dec 30, 2025 82
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 21/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመ ጀምሮ ባከናወናቸው ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ሀገራዊ ምክክሩን ለመምራት ገለልተኛ ሆኖ መዋቀሩን ያስገነዘቡት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቃል አቀባይ ጥበቡ ታደሰ፤ እስካሁን ስኬታማ ተግባራት ማከናወኑን ለኢዜአ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ባለድርሻ አካላት ተለይተው በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ በማድረግ ረገድ በርካታ ውጤቶች የተገኙባቸው ሥራዎች ተሠርተዋል ብለዋል። አጀንዳ የተሰበሰበበት መንገድ በርካቶች የተስተናገዱባቸው መድረኮች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህም የዴሞክራሲ ልምምድን በማሳደግ የምክክር ሂደት እንዲዳብር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። የምክክር ሂደቱ የኢትዮጵያውያን እንዲሆንና ባለድርሻ አካላት የሂደቱ ባለቤት እንዲሆኑ የተሠሩ ሥራዎችም ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን ነው ያስገነዘቡት። በግልጽና ገለልተኛ አሠራር አካታችና አሳታፊ በሆነ መንገድ ተሳታፊዎችን መለየት መቻሉ ከተገኙ ውጤቶች መካከል መሆኑንም ጠቁመዋል። በውክልና የመሳተፍ ልምምዶችን፣ዴሞክራሲያዊ ባሕርይን የማምጣቱ ጉዳይም ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው መሆኑን አመላክተው፤ 93 በመቶ የኢትዮጵያ ወረዳዎችን በምክክር ሂደቱ ማሳተፍ መቻሉን አመላክተዋል። በሕዝቡ፣በባለድርሻ አካላት፣ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡም ጭምር ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ተቀባይነት እንዲኖረው የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት መሆኑንም ነው ያረጋገጡት። በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት እንደተጠበቁ ሆነው በሂደት ከኃይል አማራጭ ይልቅ ምክክር የተሻለ ውጤታማ ያደርጋል የሚለው አስተሳሰብ በበርካቶች ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ባለፉት ጊዜያት የተደረጉ ጥረቶች ውጤት ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል። ኮሚሽኑ በቅርቡም በትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት እንደሚያካሂድ ገልጸው፥ በተቀሩት ሁሉም ክልሎች፣በአዲስ አበባ ከተማ፣ በድሬዳዋ አሥተዳደር፣ በዳያስፖራው ማኅበረሰብ እና በፌደራል ደረጃ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ተግባራት በስኬት መከናወናቸውንም አክለዋል።
የሚታይ
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል
Dec 30, 2025 100
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ጠንካራ የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ለዚህም አካታች ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማከናወን፣ የህግ የበላይነት የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት እንዲሁም ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የረጅም ዓመት ታሪክ ውስጥ ብሔራዊ መግባባት አለመስፈን፣ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ አለመፍታት እና ኋላ ቀር የፖለቲካ አመለካከት በሀገረ መንግስቱ ውስጥ የታዩ ስብራቶች መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደትን ማሳካት፣ ምርጫን በተሳካ መንገድ ማካሄድ፣ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የምትሆን ሀገር ለመገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ውጤታማ መሆን የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚፈታ የገለጹት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያን ስብራቶች ከመጠገን አኳያም ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባት ወሣኝ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባት ለመፍጠር ስለሚያግዝ ሁሉም በንቃት መሳተፍ እንዳለበት ጠቅሰው፤ ለግጭት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታትም ትክክለኛ አማራጭ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ሀገራዊ ምክክር ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት መሰረት በሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ብለዋል። የተሳካ ሀገራዊ ምክክር ማከናወን ሁሉም ዜጎች የተግባቡበት የጋራ ሕገ-መንግስት እውን ለማድረግና ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ስለሚረዳ የሁሉንም የነቃ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ነው የተናገሩት። በኢትዮጵያ ኋላቀር የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር፣ አዎንታዊ የሰላም ባህልን ለመገንባት እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብቶቻቸው ሰርተው እንዲለወጡና የበለጸገች ሀገር እንዲገነቡ መሰረት ይጥላል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብና የተሳታፊዎች ልየታ ለማከናወን የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም ከክልሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶች መደረጋቸውን ለምክር ቤቱ ከቀረቡ ሪፖርቶች መገንዘብ እንደሚቻል ተናግረዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ
Dec 30, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዷል። የአዋጁን አስፈላጊነትም የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት እንዲሁም የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች በጋራ ያዘጋጁት ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቧል።   በምክር ቤቱ የሁለቱን ቋሚ ኮሚቲ የውሳኔ ሃሳብ ሪፖርትም የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፈቲያ አህመድ አቅርበዋል፡፡ በሪፖርቱም ረቂቅ አዋጁ የሥርዓተ ምኅዳር ደኅንነትና ዘላቂነትን በማረጋገጥ ጥቅምና የተፈጥሮ አያያዝን ለማሻሻል ወሳኝ መሆኑን በሪፖርታቸው አመላክተዋል። በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ዋጋ ላይ የተፈጠረው ሳይንሳዊ ግንዛቤ ማደግ ለአዋጁ መውጣት መነሻ ምክንያት መሆኑንም አስረድተዋል። የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎቶች ለኢኮኖሚ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ በፖሊሲዎችና በውሳኔ አሰጣጥ ላይ እየተንጸባረቀ የሚገኝ መሆኑም ተገልጿል።   በዚህም የሥርዓተ ምኅዳርን በዘላቂነት ለማስተዳደር የሚያስችል የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ የሕግ ማዕቀፍና የአሰራር ስርዓቶችን መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ በረቂቅ አዋጁ የውሳኔ ሀሳብ ገልጸዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም፤ በረቂቅ አዋጁ ላይ ቢሻሻሉና ቢካተቱ ያሏቸውን ምክረ ሃሳቦች በጥያቄና አስተያየት አቅርበዋል። በቀጣይም የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ የትግበራ አፈፃጸም ውጤታማነትን ለማስጠበቅ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በመጨረሻም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ስብሰባው የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን በመመርመር በአዋጅ ቁጥር 1401/2018 ዓ.ም በአንድ ድምፅ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡
የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም በከተሞች መካከል ጤናማ የውድድር መንፈስ እንዲፈጠር አስችሏል 
Dec 30, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም በሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች መካከል ጤናማ የውድድር መንፈስ እንዲፈጠር ማስቻሉን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ። “የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት” በሚል መሪ ቃል 10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም በቅርቡ በአፋር ክልል ሰመራ-ሎጊያ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል። ፎረሙ ከተሞች ልምድ እንዲለዋወጡ፣ ራሳቸውን እንዲያስተዋውቁ እና ለሀገር ዕድገት ያላቸውን ሚና እንዲፈትሹ የሚያስችል ሰፊ መድረክ መሆኑም ተመልክቷል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ፎረሙ ከተሞች እንዲነቃቁ በማድረግ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በተጨማሪም በከተሞች መካከል ያለውን ትስስር በማጠናከር ለሕዝቦች አብሮነትና ለሀገራዊ ትርክት ግንባታ ገንቢ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቁመዋል። ከተሞች በራሳቸው ጸጋ የማደግ ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልጸው፤ የመደመር መንግሥት ከተሞችን የድህነትና የመልካም አስተዳደር እጦት ማሳያ ከመሆን አውጥቶ የብልጽግና ማዕከልና ተምሳሌት ለማድረግ በትኩረት እየሠራ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህ እሳቤ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችም የኢትዮጵያን አዲስ ከፍታ የሚያሳዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት ከተሞችን የመለወጥ ራዕይ በተግባር እየተገለጠ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡ ስትራቴጂ በመንደፍና በፖሊሲ በመደገፍ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ከተሞች የብልጽግና ተምሳሌት እንዲሆኑ እየተሠራ መሆኑን አመልክተዋል።
የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ተዓማኒ፣ ጥራት ያለውና ጊዜውን የጠበቀ የጤና መረጃ ለማግኘት ያስችላል
Dec 30, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ተዓማኒ፣ ጥራት ያለውና ጊዜውን የጠበቀ የጤና መረጃ ማግኘት የሚያስችል መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ገለጹ፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አዋጅን አተገባበር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።   የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 1370/2017 መሰረት ከፌደራል እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን ራሱን የቻለ አደረጃጀት እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዚህም አገልግሎቱ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የማከናወን፣ የመምራት፣ የማስተባበር፣ የመደገፍ፣ የምዝገባ መረጃዎችን የማስተዳደር እና የማደራጀት፣ በብሔራዊ ደረጃ በመረጃ ቋት አደራጅቶ የመያዝ ሀላፊነት ተሰጥቶታል። አዋጁ ዜጎች በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ የሚያገኙትን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ደህንነት ለማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑ ታምኖበት ተዘጋጅቷል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የጤና ተቋማትን ብሔራዊ ማንነት ማዕከል የሚያደርግ ነው፡፡ በጤና ተቋማት የልደትና ሞት ምዝገባ እንደሚከናወን ገልጸው፤ ምዝገባው በዲጂታል የተደገፈ መሆኑ የተጣራ የጤና መረጃ ማግኘት ያስችላል ብለዋል፡፡ በሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የሚገኘው የጤና መረጃ ለተወለዱ ህፃናት የሚያስፈልገው የክትባት፣ የሥነ ምግብ አልያም የክትትል ሥርዓቱ ምን መምሰል እንዳለበት ማወቅ እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ለእናቶች የሚያስፈልገውን አገልግሎት መለየት ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ በሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የሞት መንስኤዎችን መለየት የሚያስችል መረጃ እንደሚሰጥ የገለጹት ዶክተር ደረጀ፤ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃፀም መገምገም ያስችላል ብለዋል፡፡ የተደራጀ የዲጂታል ምዝገባ በማካሄድ ተዓማኒ፣ ጥራት ያለውና ጊዜውን የጠበቀ የጤና መረጃ ማግኘት እንደሚያስችልም ተናግረዋል፡፡ የጤና ፕሮግራሞችን ተፈፃሚነት ለመከታተል፣ እቅዶችን ለማውጣት እና ሥራዎችን ለመገምገም አስፈላጊ የመረጃ ምንጭ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የባሕል ፍርድ ቤቶች ስራ መጀመር የማሕበረሰቡ ነባር እሴት እንዲጠናከር ያግዛሉ
Dec 30, 2025 82
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የባሕል ፍርድ ቤቶች እውቅና አግኝተው ስራ መጀመራቸው የማሕበረሰቡ ነባር እሴት እንዲጠናከር እንደሚያግዙ ተመላከተ። የክልሉ የባሕል ፍርድ ቤቶች እውቅና አሰጣጥና ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የክልሉና የፌደራል ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በባሕርዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።   በመርሃ ግብሩ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የባሕል ፍርድ ቤቶች የማሕበረሰቡን ችግር በመፍታት ዘመናትን የተሻገሩ እሴቶች በመሆናቸው እንዲጠናከሩ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሚና በመረዳት ሕጋዊ እውቅና ተሰጥቷቸው እንዲሰሩ ማድረጉ ችግሮችን በጥበብና በብልሃት ለማለፍ የሚያግዝ ነው ብለዋል። የባሕል ፍርድ ቤቶቹ አቅመ ደካማ የሕብረተሰብ ክፍሎች በቅርበት ፍትሕ እንዲያገኙ በማገዝ ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አንስተዋል።   የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች ማሕበረሰቡ የሚያጋጥመውን ችግር የሚፈታበት ከጥንት ጀምሮ ይዞት የመጣ የሽምግልና ስርዓት እንዳለው ገልጸዋል። ይህን አሰራር በባሕል ፍርድ ቤቶች በሕግ አግባብ በማደራጀትና ሕጋዊ እውቅና በመስጠት ወደ ስራ ማስገባት መቻሉ የሚበረታታ ነው ብለዋል። ይሕም መንግስት ችግሮችን በንግግርና በውይይት በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የያዘውን ግብ ለማሳካት እንደሚያግዝ ተናግረዋል። በየአካባቢው ሴቶች፣ ሕጻናትና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን መብትና ጥቅም በማስከበር በኩልም ሚና ይኖራቸዋል ነው ያሉት። የአማራ ክልል መንግስት ወደ ስራ ላስገባቸው የባሕል ፍርድ ቤቶች ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።   የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር ለባሕል ፍርድ ቤቶች መጎልበት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በክልሎች ለባሕል ፍርድ ቤቶች የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። ባሕልን መሰረተ ያደረገ የግጭት አፈታት አሰራርን ለማጎልበት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አለምአንተ አግደው ናቸው።   የክልሉ መንግስት የባሕል ፍርድ ቤቶችን በሕግ አግባብ በማደራጀትና አሰራር በማበጀት ወደ ስራ የሚገቡበትን ሁኔታ ሲያመቻች መቆየቱን አንስተዋል። ሽምግልናን ጨምሮ 15 ሌሎች ማህበራዊ እሴቶች በክልሉ የባሕል ፍርድ ቤቶች እውቅና እንዲሰጣቸው መደረጉን ጠቁመው፤ የባሕል ፍርድ ቤቶቹ ተጠሪነታቸው ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ባሕላዊ ፍርድ ቤቶቹ በአካባቢያቸው ባሕልና ወግ መሰረት ሕብረተሰቡን እንዲያገለግሉ የሚያስችል መሆኑን በማብራራት።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል-ኮሚሽኑ
Dec 30, 2025 82
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 21/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመ ጀምሮ ባከናወናቸው ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ሀገራዊ ምክክሩን ለመምራት ገለልተኛ ሆኖ መዋቀሩን ያስገነዘቡት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቃል አቀባይ ጥበቡ ታደሰ፤ እስካሁን ስኬታማ ተግባራት ማከናወኑን ለኢዜአ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ባለድርሻ አካላት ተለይተው በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ በማድረግ ረገድ በርካታ ውጤቶች የተገኙባቸው ሥራዎች ተሠርተዋል ብለዋል። አጀንዳ የተሰበሰበበት መንገድ በርካቶች የተስተናገዱባቸው መድረኮች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህም የዴሞክራሲ ልምምድን በማሳደግ የምክክር ሂደት እንዲዳብር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። የምክክር ሂደቱ የኢትዮጵያውያን እንዲሆንና ባለድርሻ አካላት የሂደቱ ባለቤት እንዲሆኑ የተሠሩ ሥራዎችም ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን ነው ያስገነዘቡት። በግልጽና ገለልተኛ አሠራር አካታችና አሳታፊ በሆነ መንገድ ተሳታፊዎችን መለየት መቻሉ ከተገኙ ውጤቶች መካከል መሆኑንም ጠቁመዋል። በውክልና የመሳተፍ ልምምዶችን፣ዴሞክራሲያዊ ባሕርይን የማምጣቱ ጉዳይም ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው መሆኑን አመላክተው፤ 93 በመቶ የኢትዮጵያ ወረዳዎችን በምክክር ሂደቱ ማሳተፍ መቻሉን አመላክተዋል። በሕዝቡ፣በባለድርሻ አካላት፣ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡም ጭምር ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ተቀባይነት እንዲኖረው የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት መሆኑንም ነው ያረጋገጡት። በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት እንደተጠበቁ ሆነው በሂደት ከኃይል አማራጭ ይልቅ ምክክር የተሻለ ውጤታማ ያደርጋል የሚለው አስተሳሰብ በበርካቶች ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ባለፉት ጊዜያት የተደረጉ ጥረቶች ውጤት ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል። ኮሚሽኑ በቅርቡም በትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት እንደሚያካሂድ ገልጸው፥ በተቀሩት ሁሉም ክልሎች፣በአዲስ አበባ ከተማ፣ በድሬዳዋ አሥተዳደር፣ በዳያስፖራው ማኅበረሰብ እና በፌደራል ደረጃ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ተግባራት በስኬት መከናወናቸውንም አክለዋል።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል
Dec 30, 2025 100
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ጠንካራ የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ለዚህም አካታች ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማከናወን፣ የህግ የበላይነት የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት እንዲሁም ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የረጅም ዓመት ታሪክ ውስጥ ብሔራዊ መግባባት አለመስፈን፣ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ አለመፍታት እና ኋላ ቀር የፖለቲካ አመለካከት በሀገረ መንግስቱ ውስጥ የታዩ ስብራቶች መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደትን ማሳካት፣ ምርጫን በተሳካ መንገድ ማካሄድ፣ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የምትሆን ሀገር ለመገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ውጤታማ መሆን የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚፈታ የገለጹት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያን ስብራቶች ከመጠገን አኳያም ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባት ወሣኝ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባት ለመፍጠር ስለሚያግዝ ሁሉም በንቃት መሳተፍ እንዳለበት ጠቅሰው፤ ለግጭት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታትም ትክክለኛ አማራጭ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ሀገራዊ ምክክር ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት መሰረት በሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ብለዋል። የተሳካ ሀገራዊ ምክክር ማከናወን ሁሉም ዜጎች የተግባቡበት የጋራ ሕገ-መንግስት እውን ለማድረግና ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ስለሚረዳ የሁሉንም የነቃ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ነው የተናገሩት። በኢትዮጵያ ኋላቀር የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር፣ አዎንታዊ የሰላም ባህልን ለመገንባት እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብቶቻቸው ሰርተው እንዲለወጡና የበለጸገች ሀገር እንዲገነቡ መሰረት ይጥላል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብና የተሳታፊዎች ልየታ ለማከናወን የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም ከክልሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶች መደረጋቸውን ለምክር ቤቱ ከቀረቡ ሪፖርቶች መገንዘብ እንደሚቻል ተናግረዋል።
የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር የተጀመሩ ተግባራት ስኬታማ እንዲሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ማጎልበት ይጠበቅባቸዋል
Dec 30, 2025 109
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር የተጀመሩ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ሀላፊ ሞገስ ባልቻ ገለጹ። በ"ዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አባበ ለሚገኙ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስልጠና እየተሰጠ ነው።   በስልጠና መርሃ ግብሩ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ከተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ሀላፊ ሞገስ ባልቻ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግስት ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው። ለዚህም ጠንካራ ተቋማት አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለተቋማቱ መጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተዋል። የሀገር ግንባታ ሂደት የሚሳካው በኃይልና በግጭት ሳይሆን፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይትና ምክክር በመፍታትና ለሃሳብ የበላይነት ተገዢ በመሆን ነው ብለዋል። መሰል የዲሞክራሲ ልምምድ እንዲጎለብት የሲቪል ማህበራት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። መንግሥት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት መድረክ መመስረቱን ተናግረዋል። ይሄ መድረክ በአዲስ አበባ ደረጃም መመስረቱን አስታውሰው፤ በዚህ መድረክ ላይም በአዲስ አበባ ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ ገልፀዋል።   በአዲስ አበባ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ ሚኤሳ ኤሌማ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ስልጠናው በመዲናዋ ያሉ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ይበልጥ ለማጉላት ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመንግሥት እና በድርጅቶች መካከል ይበልጥ ተቀራርቦ ለህዝብ ጥቅም መስራት ሌላው የስልጠናው ዓላማ መሆኑንም አብራርተዋል።
በክልሉ ሰላምን ጠብቆ በማዝለቅ ለልማት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 29, 2025 188
ባሕር ዳር፤ ታሕሳስ 20/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የሰፈነውን ሰላም ጠብቆ በማዝለቅ ለልማት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ። የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ በክልሉ ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማፋጠን በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በየደረጃው የሚገኙ የሚሊሻና የሰላም አስከባሪዎች ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ሰላምን ከማስከበራቸው ጎን ለጎን በልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ሲያከናውኑ እንደቆዩ አንስተዋል። ጠንካራ የሕግ ማስክበር ስራ በማከናወን ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል። ተግባሩን በማጠናከርም የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረትመሰጠቱን ገልጸው፤ በተለይም የክልሉ የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት ዕቅድ ውጤታማ እንዲሆን በጠንካራ አደረጃጀት ሰላም ማስፈን ላይ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም የተቋሙን አደረጃጀት ቀደም ሲል ከነበረበት የጽሕፈት ቤት ደረጃ ወደ ኮሚሽንነት መሸጋገሩን አንስተው፤ የሕግ ማስከበር ሥራውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየተመራ መሆኑን አንስተዋል። የሰላም አማራጭን በመከተል ባለፉት ጊዜያት የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሀድሶ ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ማህበረሰቡ እየተቀላቀሉ መሆኑን አብራርተዋል። የቀሩ ታጣቂዎች ከጥፋታቸው ተመልሰው የበደሉትን ሕዝብ እንዲክሱ አሁንም መንግስት በሆደ ሰፊነት የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል። የሰላም አማራጩን ባልተቀበሉት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል።
የትህነግ ቡድን የመልሶ ማቋቋም ሥራን በማደናቀፍ ተፈናቃዮችን የፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረገ ነው-የስምረት ለዲሞክራሲ ፓርቲ
Dec 28, 2025 285
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 19/2018 (ኢዜአ)፡-የትህነግ ቡድን የመልሶ ማቋቋም ሥራን በማደናቀፍ ተፈናቃዮችን የሴራ ፖለቲካው መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን የስምረት ለዲሞክራሲ ፓርቲ ገለጸ። ሕገ ወጥ ቡድኑ የእርዳታ እህል ለተፈናቃዮች እንዳይደርስ በማድረግ ረሃብ ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን አመልክቷል። የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ አባል ጣዓመ ዓረዶም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፥ በትግራይ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ሕገወጥ ቡድን ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዳይቋቋሙ እንቅፋት ፈጥሯል። ተፈናቃዮችንም የሴራ ፖለቲካው መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሕገወጥ ቡድኑ ለፖለቲካ ትርፍ ሲል በተፈናቃዮች ስም እንደሚነግድ አመልክተው፤ ተፈናቃዮችን በማስፈራራትና ችግር ውስጥ በማስገባት ለርሃብ እየዳረገ መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሕገ ወጥ ቡድኑ ለተፈናቃዮች የሚላከውን እርዳታ በመቀማት ለፖለቲካ ዓላማ እያዋለው እንደሚገኝ አመልክተው፤ መብታቸውን የሚጠይቁትን ደግሞ እያስፈራራ ጉዳት እያደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል በተለይም በመጠለያ ጣቢያዎች እየደረሰ ያለው አስከፊ ችግር ሕገ ወጥ ቡድኑ በሴራ የፈጠረው መሆኑን አብራርተዋል። ይህ ሕገ ወጥ ቡድን የተፈናቃዩቹ ችግር፣ሞትና ስቃይ እንዲቀጥል እያደረገ ነው ያሉት አቶ ጣዓመ፤ በተለይም ወደ ክልሉ የሚገባውን ሰብዓዊ እርዳታና ቁሳቁስ ለተረጂዎች በቀጥታ መድረሱን በተለያየ አካላት ማረጋገጥ እንደሚገባ አመልክተዋል። ሕገ ወጥ ቡድኑ የሴራ ፖለቲካውን ለማራመድ ሲል በጭካኔ በትግራይ ችግር እንዲቀጥል እያደረገ መሆኑንም አንስተዋል። የፌዴራል መንግስት በመጠለያ ጣቢያዎች ለተፈናቃዮች እያደረገ ያለውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን ሀገራዊ ምክክሩ ወርቃማ ዕድል ነው
Dec 28, 2025 255
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 19/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን የሀገራዊ ምክክሩ ያስገኘውን ወርቃማ ዕድል ሁሉም ዜጋ ሊጠቀምበት እንደሚገባ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን የማደራጀትና ግብዓቶችን የማሰባሰብ ተግባራት በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ማሳወቁ ይታወሳል። የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አህመድ ሁሴን፤ ኢትዮጵያዊያን ምክክር በማድረግ በጋራ አጀንዳዎች ላይ መግባባት ባለመፍጠራቸው ሀገር ዋጋ ስትከፍል መቆየቷን ገልጸዋል። በዚህም መነሻነት ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት ሲንከባለሉ በቆዩ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ወርቃማ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያም በሃሳብ የበላይነት የተመሠረተ ሀገራዊ ምክክር በማካሄድ ብሔራዊ መግባባትን ማጠናከር የሚያስችል የዳበረ የዴሞክራሲ ሥርዓትና የፖለቲካ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሀገራዊ ምክክር አሳታፊ፣ አካታችና ተዓማኒነት ለማስጠበቅ በተከናወኑ የቅድመ ጉባኤ ምክክር ሂደቶች ላይ አዎንታዊ ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። ብሄራዊ መግባባትን ለማጠናከርና አንድነትን ለማጽናት ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ዕድል መሆኑንም አመልክተዋል። በቀጣይ ብሔራዊ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የተፈጠረውን የሀገራዊ ምክክር ዕድል ሁሉም ዜጋ ሊጠቀምበት እንደሚገባ አስረድተዋል።   የተርካንፊ ሰስተነብል ዴቨሎፕመንት መስራችና ዳይሬክተር ወርቅነሽ ቤጊ፤ በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሂደት የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ሴቶች በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ብሔራዊ መግባባት የሚሹ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ተናግረዋል።   የዋይቡንቱ ዪዝ ፒስ ቢወልዲንግ አሊያንስ ፀሐፊ ሲሳይ ታረቀኝ፥ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደትም የወጣቶችን የነቃ ተሳትፎ የሚያረጋግጡ ተግባራትን እያከናወኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። በቀጣይም ለዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የመደመር መንግስት እሳቤን በመተግበር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቷል
Dec 27, 2025 244
ደብረ ማርቆስ/ገንዳ ውሃ/ወልዲያ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-የመደመር መንግስት እሳቤን በመተግበር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማጠናከር ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ። በደብረ ማርቆስ፣ ገንዳ ውሃና በወልዲያ ከተሞች "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል ሃሳብ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉባቸው የውይይት መድረኮች ተካሂደዋል። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በተካሄደ መድረክ ላይ የአስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ እንደገለጹት፤ የመደመር መንግስት በወል ትርክት ላይ የተመሰረተ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት እየሰራ ነው።   ለዚህም የቀደመ መልካም እሴቶች ላይ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት ግብ ተይዞ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማ አስተዳደሩ በመንገድ፣ በኢንዱስትሪ፣ በሃይል አቅርቦትና ሌሎች መሰል መሰረተ ልማቶች ማተኮሩንም ገልጸዋል። ከልማት ሥራዎች በተጓዳኝ በአካባቢው ሰላምን አጠናክሮ ለማስቀጠል ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ነው ያስረዱት።   የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ህዝብን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአካባቢን ሀብት ለይቶ ማልማት ከተቻለ ድህነትን ማሸነፍ እንደሚቻል ትምህርት የተገኘባቸው ናቸው ብለዋል። በመደመር መንግስት በልማትና በመልካም አስተዳደር የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ሥራዎች ይጠናከራሉ ያሉት ደግሞ በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ የተገኙት የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ ናቸው።   በዞኑ ያሉትን ፀጋዎች አልምቶ ለህዝብ ጥቅም ለማዋል ሰላምን ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ለዚህም በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ አብዱልከሪም ሙሀመድ በበኩላቸው፤ በመደመር መንግስት እሳቤ በከተማዋ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት እየተሰራ ነው። የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በአገር አቀፍ ደረጃ በስኬት የተጠናቀቁ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የመንግስትን የልማት ቁርጠኝነት ያሳያሉ።   የመደመር መንግስት እሳቤዎችን ለማሳካት በሰላምና ልማት ግንባታ ላይ ህዝብን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ናቸው። ህዝቡም ሠላምና ልማትን የሚያደናቅፉ አካላትን በአደባባይ ጭምር ማውገዙን አስታውሰው ይህም ተጠናክሮ መጠቀል እንዳለበት አሳስበዋል።   የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በአካባቢው የሰፈነው ሠላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡ አድርገዋል። በየከተሞቹ በተካሄደ የውይይት መድረክ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን- የምክር ቤት አባላት
Dec 27, 2025 238
ባሕርዳር ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው ከምክር ቤቱ አባላት መካከል ከሰሜን ጎንደር ዞን ድልይብዛ ምርጫ ክልል የተወከሉት አቶ ብርሃኑ ዘውዱ ፤ በክልሉ ሰላምን ለማዝለቅ የሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎና ድጋፍ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል።   ‎‎‎ችግር በውይይት እንጂ በግጭት እንደማይፈታ በመገንዘብ የቀሩ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተከትለው እንዲመለሱ መክረዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ ‎‎የክልሉን ሰላም በማዝለቅ ልማቱ ይበልጥ እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ‎‎ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ምርጫ ክልል በምክር ቤቱ የተወከሉት ወይዘሮ ፋጡማ ይማም በበኩላቸው፤ ሰላምን ለማዝለቅ የምክር ቤት አባላት ድርብ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።   ‎አሁን በክልሉ የሰፈነውን ሰላም ለማዝለቅ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ድጋፍና ክትትላቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል አቶ አሰፋ ይመር፤ የሰላም አማራጭን ተከትለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች እንደሚበረታቱና ይህም ሰላምን ለማፅናት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።   ‎የቀሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ የተጀመረውን ስራ ለማጠናከር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
ፖለቲካ
እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል-ኮሚሽኑ
Dec 30, 2025 82
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 21/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመ ጀምሮ ባከናወናቸው ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ሀገራዊ ምክክሩን ለመምራት ገለልተኛ ሆኖ መዋቀሩን ያስገነዘቡት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቃል አቀባይ ጥበቡ ታደሰ፤ እስካሁን ስኬታማ ተግባራት ማከናወኑን ለኢዜአ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ባለድርሻ አካላት ተለይተው በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ በማድረግ ረገድ በርካታ ውጤቶች የተገኙባቸው ሥራዎች ተሠርተዋል ብለዋል። አጀንዳ የተሰበሰበበት መንገድ በርካቶች የተስተናገዱባቸው መድረኮች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህም የዴሞክራሲ ልምምድን በማሳደግ የምክክር ሂደት እንዲዳብር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። የምክክር ሂደቱ የኢትዮጵያውያን እንዲሆንና ባለድርሻ አካላት የሂደቱ ባለቤት እንዲሆኑ የተሠሩ ሥራዎችም ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን ነው ያስገነዘቡት። በግልጽና ገለልተኛ አሠራር አካታችና አሳታፊ በሆነ መንገድ ተሳታፊዎችን መለየት መቻሉ ከተገኙ ውጤቶች መካከል መሆኑንም ጠቁመዋል። በውክልና የመሳተፍ ልምምዶችን፣ዴሞክራሲያዊ ባሕርይን የማምጣቱ ጉዳይም ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው መሆኑን አመላክተው፤ 93 በመቶ የኢትዮጵያ ወረዳዎችን በምክክር ሂደቱ ማሳተፍ መቻሉን አመላክተዋል። በሕዝቡ፣በባለድርሻ አካላት፣ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡም ጭምር ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ተቀባይነት እንዲኖረው የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት መሆኑንም ነው ያረጋገጡት። በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት እንደተጠበቁ ሆነው በሂደት ከኃይል አማራጭ ይልቅ ምክክር የተሻለ ውጤታማ ያደርጋል የሚለው አስተሳሰብ በበርካቶች ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ባለፉት ጊዜያት የተደረጉ ጥረቶች ውጤት ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል። ኮሚሽኑ በቅርቡም በትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት እንደሚያካሂድ ገልጸው፥ በተቀሩት ሁሉም ክልሎች፣በአዲስ አበባ ከተማ፣ በድሬዳዋ አሥተዳደር፣ በዳያስፖራው ማኅበረሰብ እና በፌደራል ደረጃ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ተግባራት በስኬት መከናወናቸውንም አክለዋል።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል
Dec 30, 2025 100
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ጠንካራ የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ለዚህም አካታች ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማከናወን፣ የህግ የበላይነት የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት እንዲሁም ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የረጅም ዓመት ታሪክ ውስጥ ብሔራዊ መግባባት አለመስፈን፣ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ አለመፍታት እና ኋላ ቀር የፖለቲካ አመለካከት በሀገረ መንግስቱ ውስጥ የታዩ ስብራቶች መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደትን ማሳካት፣ ምርጫን በተሳካ መንገድ ማካሄድ፣ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የምትሆን ሀገር ለመገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ውጤታማ መሆን የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚፈታ የገለጹት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያን ስብራቶች ከመጠገን አኳያም ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባት ወሣኝ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባት ለመፍጠር ስለሚያግዝ ሁሉም በንቃት መሳተፍ እንዳለበት ጠቅሰው፤ ለግጭት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታትም ትክክለኛ አማራጭ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ሀገራዊ ምክክር ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት መሰረት በሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ብለዋል። የተሳካ ሀገራዊ ምክክር ማከናወን ሁሉም ዜጎች የተግባቡበት የጋራ ሕገ-መንግስት እውን ለማድረግና ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ስለሚረዳ የሁሉንም የነቃ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ነው የተናገሩት። በኢትዮጵያ ኋላቀር የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር፣ አዎንታዊ የሰላም ባህልን ለመገንባት እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብቶቻቸው ሰርተው እንዲለወጡና የበለጸገች ሀገር እንዲገነቡ መሰረት ይጥላል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብና የተሳታፊዎች ልየታ ለማከናወን የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም ከክልሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶች መደረጋቸውን ለምክር ቤቱ ከቀረቡ ሪፖርቶች መገንዘብ እንደሚቻል ተናግረዋል።
የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር የተጀመሩ ተግባራት ስኬታማ እንዲሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ማጎልበት ይጠበቅባቸዋል
Dec 30, 2025 109
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር የተጀመሩ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ሀላፊ ሞገስ ባልቻ ገለጹ። በ"ዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አባበ ለሚገኙ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስልጠና እየተሰጠ ነው።   በስልጠና መርሃ ግብሩ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ከተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ሀላፊ ሞገስ ባልቻ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግስት ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው። ለዚህም ጠንካራ ተቋማት አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለተቋማቱ መጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተዋል። የሀገር ግንባታ ሂደት የሚሳካው በኃይልና በግጭት ሳይሆን፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይትና ምክክር በመፍታትና ለሃሳብ የበላይነት ተገዢ በመሆን ነው ብለዋል። መሰል የዲሞክራሲ ልምምድ እንዲጎለብት የሲቪል ማህበራት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። መንግሥት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት መድረክ መመስረቱን ተናግረዋል። ይሄ መድረክ በአዲስ አበባ ደረጃም መመስረቱን አስታውሰው፤ በዚህ መድረክ ላይም በአዲስ አበባ ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ ገልፀዋል።   በአዲስ አበባ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ ሚኤሳ ኤሌማ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ስልጠናው በመዲናዋ ያሉ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ይበልጥ ለማጉላት ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመንግሥት እና በድርጅቶች መካከል ይበልጥ ተቀራርቦ ለህዝብ ጥቅም መስራት ሌላው የስልጠናው ዓላማ መሆኑንም አብራርተዋል።
በክልሉ ሰላምን ጠብቆ በማዝለቅ ለልማት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 29, 2025 188
ባሕር ዳር፤ ታሕሳስ 20/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የሰፈነውን ሰላም ጠብቆ በማዝለቅ ለልማት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ። የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ በክልሉ ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማፋጠን በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በየደረጃው የሚገኙ የሚሊሻና የሰላም አስከባሪዎች ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ሰላምን ከማስከበራቸው ጎን ለጎን በልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ሲያከናውኑ እንደቆዩ አንስተዋል። ጠንካራ የሕግ ማስክበር ስራ በማከናወን ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል። ተግባሩን በማጠናከርም የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረትመሰጠቱን ገልጸው፤ በተለይም የክልሉ የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት ዕቅድ ውጤታማ እንዲሆን በጠንካራ አደረጃጀት ሰላም ማስፈን ላይ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም የተቋሙን አደረጃጀት ቀደም ሲል ከነበረበት የጽሕፈት ቤት ደረጃ ወደ ኮሚሽንነት መሸጋገሩን አንስተው፤ የሕግ ማስከበር ሥራውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየተመራ መሆኑን አንስተዋል። የሰላም አማራጭን በመከተል ባለፉት ጊዜያት የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሀድሶ ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ማህበረሰቡ እየተቀላቀሉ መሆኑን አብራርተዋል። የቀሩ ታጣቂዎች ከጥፋታቸው ተመልሰው የበደሉትን ሕዝብ እንዲክሱ አሁንም መንግስት በሆደ ሰፊነት የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል። የሰላም አማራጩን ባልተቀበሉት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል።
የትህነግ ቡድን የመልሶ ማቋቋም ሥራን በማደናቀፍ ተፈናቃዮችን የፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረገ ነው-የስምረት ለዲሞክራሲ ፓርቲ
Dec 28, 2025 285
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 19/2018 (ኢዜአ)፡-የትህነግ ቡድን የመልሶ ማቋቋም ሥራን በማደናቀፍ ተፈናቃዮችን የሴራ ፖለቲካው መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን የስምረት ለዲሞክራሲ ፓርቲ ገለጸ። ሕገ ወጥ ቡድኑ የእርዳታ እህል ለተፈናቃዮች እንዳይደርስ በማድረግ ረሃብ ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን አመልክቷል። የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ አባል ጣዓመ ዓረዶም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፥ በትግራይ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ሕገወጥ ቡድን ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዳይቋቋሙ እንቅፋት ፈጥሯል። ተፈናቃዮችንም የሴራ ፖለቲካው መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሕገወጥ ቡድኑ ለፖለቲካ ትርፍ ሲል በተፈናቃዮች ስም እንደሚነግድ አመልክተው፤ ተፈናቃዮችን በማስፈራራትና ችግር ውስጥ በማስገባት ለርሃብ እየዳረገ መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሕገ ወጥ ቡድኑ ለተፈናቃዮች የሚላከውን እርዳታ በመቀማት ለፖለቲካ ዓላማ እያዋለው እንደሚገኝ አመልክተው፤ መብታቸውን የሚጠይቁትን ደግሞ እያስፈራራ ጉዳት እያደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል በተለይም በመጠለያ ጣቢያዎች እየደረሰ ያለው አስከፊ ችግር ሕገ ወጥ ቡድኑ በሴራ የፈጠረው መሆኑን አብራርተዋል። ይህ ሕገ ወጥ ቡድን የተፈናቃዩቹ ችግር፣ሞትና ስቃይ እንዲቀጥል እያደረገ ነው ያሉት አቶ ጣዓመ፤ በተለይም ወደ ክልሉ የሚገባውን ሰብዓዊ እርዳታና ቁሳቁስ ለተረጂዎች በቀጥታ መድረሱን በተለያየ አካላት ማረጋገጥ እንደሚገባ አመልክተዋል። ሕገ ወጥ ቡድኑ የሴራ ፖለቲካውን ለማራመድ ሲል በጭካኔ በትግራይ ችግር እንዲቀጥል እያደረገ መሆኑንም አንስተዋል። የፌዴራል መንግስት በመጠለያ ጣቢያዎች ለተፈናቃዮች እያደረገ ያለውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን ሀገራዊ ምክክሩ ወርቃማ ዕድል ነው
Dec 28, 2025 255
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 19/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን የሀገራዊ ምክክሩ ያስገኘውን ወርቃማ ዕድል ሁሉም ዜጋ ሊጠቀምበት እንደሚገባ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን የማደራጀትና ግብዓቶችን የማሰባሰብ ተግባራት በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ማሳወቁ ይታወሳል። የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አህመድ ሁሴን፤ ኢትዮጵያዊያን ምክክር በማድረግ በጋራ አጀንዳዎች ላይ መግባባት ባለመፍጠራቸው ሀገር ዋጋ ስትከፍል መቆየቷን ገልጸዋል። በዚህም መነሻነት ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት ሲንከባለሉ በቆዩ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ወርቃማ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያም በሃሳብ የበላይነት የተመሠረተ ሀገራዊ ምክክር በማካሄድ ብሔራዊ መግባባትን ማጠናከር የሚያስችል የዳበረ የዴሞክራሲ ሥርዓትና የፖለቲካ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሀገራዊ ምክክር አሳታፊ፣ አካታችና ተዓማኒነት ለማስጠበቅ በተከናወኑ የቅድመ ጉባኤ ምክክር ሂደቶች ላይ አዎንታዊ ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። ብሄራዊ መግባባትን ለማጠናከርና አንድነትን ለማጽናት ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ዕድል መሆኑንም አመልክተዋል። በቀጣይ ብሔራዊ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የተፈጠረውን የሀገራዊ ምክክር ዕድል ሁሉም ዜጋ ሊጠቀምበት እንደሚገባ አስረድተዋል።   የተርካንፊ ሰስተነብል ዴቨሎፕመንት መስራችና ዳይሬክተር ወርቅነሽ ቤጊ፤ በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሂደት የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ሴቶች በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ብሔራዊ መግባባት የሚሹ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ተናግረዋል።   የዋይቡንቱ ዪዝ ፒስ ቢወልዲንግ አሊያንስ ፀሐፊ ሲሳይ ታረቀኝ፥ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደትም የወጣቶችን የነቃ ተሳትፎ የሚያረጋግጡ ተግባራትን እያከናወኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። በቀጣይም ለዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የመደመር መንግስት እሳቤን በመተግበር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቷል
Dec 27, 2025 244
ደብረ ማርቆስ/ገንዳ ውሃ/ወልዲያ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-የመደመር መንግስት እሳቤን በመተግበር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማጠናከር ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ። በደብረ ማርቆስ፣ ገንዳ ውሃና በወልዲያ ከተሞች "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል ሃሳብ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉባቸው የውይይት መድረኮች ተካሂደዋል። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በተካሄደ መድረክ ላይ የአስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ እንደገለጹት፤ የመደመር መንግስት በወል ትርክት ላይ የተመሰረተ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት እየሰራ ነው።   ለዚህም የቀደመ መልካም እሴቶች ላይ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት ግብ ተይዞ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማ አስተዳደሩ በመንገድ፣ በኢንዱስትሪ፣ በሃይል አቅርቦትና ሌሎች መሰል መሰረተ ልማቶች ማተኮሩንም ገልጸዋል። ከልማት ሥራዎች በተጓዳኝ በአካባቢው ሰላምን አጠናክሮ ለማስቀጠል ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ነው ያስረዱት።   የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ህዝብን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአካባቢን ሀብት ለይቶ ማልማት ከተቻለ ድህነትን ማሸነፍ እንደሚቻል ትምህርት የተገኘባቸው ናቸው ብለዋል። በመደመር መንግስት በልማትና በመልካም አስተዳደር የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ሥራዎች ይጠናከራሉ ያሉት ደግሞ በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ የተገኙት የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ ናቸው።   በዞኑ ያሉትን ፀጋዎች አልምቶ ለህዝብ ጥቅም ለማዋል ሰላምን ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ለዚህም በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ አብዱልከሪም ሙሀመድ በበኩላቸው፤ በመደመር መንግስት እሳቤ በከተማዋ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት እየተሰራ ነው። የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በአገር አቀፍ ደረጃ በስኬት የተጠናቀቁ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የመንግስትን የልማት ቁርጠኝነት ያሳያሉ።   የመደመር መንግስት እሳቤዎችን ለማሳካት በሰላምና ልማት ግንባታ ላይ ህዝብን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ናቸው። ህዝቡም ሠላምና ልማትን የሚያደናቅፉ አካላትን በአደባባይ ጭምር ማውገዙን አስታውሰው ይህም ተጠናክሮ መጠቀል እንዳለበት አሳስበዋል።   የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በአካባቢው የሰፈነው ሠላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡ አድርገዋል። በየከተሞቹ በተካሄደ የውይይት መድረክ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን- የምክር ቤት አባላት
Dec 27, 2025 238
ባሕርዳር ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው ከምክር ቤቱ አባላት መካከል ከሰሜን ጎንደር ዞን ድልይብዛ ምርጫ ክልል የተወከሉት አቶ ብርሃኑ ዘውዱ ፤ በክልሉ ሰላምን ለማዝለቅ የሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎና ድጋፍ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል።   ‎‎‎ችግር በውይይት እንጂ በግጭት እንደማይፈታ በመገንዘብ የቀሩ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተከትለው እንዲመለሱ መክረዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ ‎‎የክልሉን ሰላም በማዝለቅ ልማቱ ይበልጥ እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ‎‎ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ምርጫ ክልል በምክር ቤቱ የተወከሉት ወይዘሮ ፋጡማ ይማም በበኩላቸው፤ ሰላምን ለማዝለቅ የምክር ቤት አባላት ድርብ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።   ‎አሁን በክልሉ የሰፈነውን ሰላም ለማዝለቅ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ድጋፍና ክትትላቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል አቶ አሰፋ ይመር፤ የሰላም አማራጭን ተከትለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች እንደሚበረታቱና ይህም ሰላምን ለማፅናት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።   ‎የቀሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ የተጀመረውን ስራ ለማጠናከር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
ማህበራዊ
የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበትን ሥርዓት እየገነባ  ይገኛል
Dec 30, 2025 48
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበትን ስርዓት እየገነባ ይገኛል ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። በባሕርዳር ከተማ 123 ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ብር በሆነ ወጪ የተገነባ የሴቶችና ህፃናት ማገገሚያ ማዕከል ዛሬ ተመርቋል። ማዕከሉን የክልሉ የጤና ፣ የሴቶች፤ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች በጋር በመተባበር እንዳስገነቡት ተገልጿል።   በምረቃው ሥነ- ሥርዓት ላይ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበት ሥርዓት እየገነባ ይገኛል። ‎በባሕርዳር ከተማ የተገነባው የማገገሚያ ማዕከልም የመደመር መንግስት በተለይ ለተጋላጭ የሕብረተሰብ ክፍሎች የሰጠው ትኩረት አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። ‎በተቋማት ትብብር በአጭር ጊዜ የተገነባው ማገገሚያ ማዕከሉ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶችና ህፃናትን ፈጥኖ በማስገባት ወደ ቀደመ ሕይወታቸው እንዲመለሱ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ‎ሚኒስቴሩ ማዕከሉ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ በቀሳቁስና ሌሎች የድጋፍ ዓይነቶች አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። ‎‎በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶችና ህፃናት እንዳያገግሙ በመደገፍ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ‎በቀጣይም ተመሳሳይ ማዕከላትን ወደ ሌሎች ከተሞች የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። ‎የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ ፤ የማዕከሉ መገንባት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።   ‎ማዕከሉ ‎በሶስት ሺህ 200 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ በሶስት ወራት ውስጥ የተገነባ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ ናቸው። በውስጡ የመኝታ፣ የሕክምና፣ የስልጠና፣ የአስተዳደርና ሌሎች አገልግሎቶች የሚሰጡ 35 ክፍሎችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል። በ‎‎ተመሳሳይም በጎንደር ከተማ መሰል ማእከል እየተገነባ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በደሴና በሌሎች ከተሞች በቀጣይ ተደራሽ ለማድረግ ቢሮው ከክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮና የከተማ አስተዳደሮች ጋር እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ‎የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)‎ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በባሕርዳር ፈለገ ሕይወት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግቢ የተቋቋመውን ሁለንተናዊ የለውጥ መሪነት ስርዓተ ፆታ እኩልነት የስልጠና ማዕከልንም ጎብኝተዋል።
ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት በተጓዳኝ ሰላምን ለማፅናት ድጋፋችንን እናጠናክራለን- አሽከርካሪዎች 
Dec 30, 2025 34
ደብረብርሃን፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት ጎን ለጎን ሰላምን ለማፅናት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የደብረ ብርሃን ከተማ የታክሲ አሽከርካሪዎች ገለጹ። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ከታክሲ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ጋር በሰላም ማስከበር ላይ ዛሬ ተወያይቷልⵆ ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ዓለሙ አሽኔ፤ በትራንስፖርት ዘርፉ ቀልጣፋ አገልግሎት ለሕብረተሰቡ ከመስጠት በተጓዳኝ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የበኩላቸውን ሲወጡ እንደቆዩ ተናግረዋል።   ይህንን በማጠናከር ከፖሊስ ጋራ በመተባበር ወንጀልን ለመከላከል በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ሸዋለም ግዛቸው በበኩላቸው፤ የከተማዋ እድገት እንዲፋጠን የትራንስፖርቱ ዘርፍ ያለውን ድርሻ ለማሳካት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። መንግስት የሚያወጣውን ደንብና መመሪያ አክብረው በመስራት በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በዘላቂነት ለማፅናት በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ በንቃት በመሳተፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል።   የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳንኤል እሸቴ በበኩላቸው፤ ከከተማው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር በተከናወነው ሕግ የማስከበር ስራ ሰላምን ማስጠበቅ መቻሉን ተናግረዋል። ሰላምን አስጠብቆ በማዝለቅ የከተማዋን ልማት ለማፋጠን እየተከናወነ ባለው ስራ ውስጥ የታክሲ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች የድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም የታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ሕገወጥነትን በመከላከል ፈጣንና ውጤታማ አገልግሎት ለሕብረተሰቡ እንዲሰጡ ለማስገንዘብ ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል።   የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ደጀኔ ልመንህ፤ የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማፅናት የነዋሪዎች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋልⵆ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች በሰላም ማስጠብቅና በወንጀል መከላከል የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ለሕብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በውይይቱ ላይ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖችን ጨምሮ ሌሎችም አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ተዓማኒ፣ ጥራት ያለውና ጊዜውን የጠበቀ የጤና መረጃ ለማግኘት ያስችላል
Dec 30, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ተዓማኒ፣ ጥራት ያለውና ጊዜውን የጠበቀ የጤና መረጃ ማግኘት የሚያስችል መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ገለጹ፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አዋጅን አተገባበር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።   የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 1370/2017 መሰረት ከፌደራል እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን ራሱን የቻለ አደረጃጀት እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዚህም አገልግሎቱ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የማከናወን፣ የመምራት፣ የማስተባበር፣ የመደገፍ፣ የምዝገባ መረጃዎችን የማስተዳደር እና የማደራጀት፣ በብሔራዊ ደረጃ በመረጃ ቋት አደራጅቶ የመያዝ ሀላፊነት ተሰጥቶታል። አዋጁ ዜጎች በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ የሚያገኙትን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ደህንነት ለማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑ ታምኖበት ተዘጋጅቷል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የጤና ተቋማትን ብሔራዊ ማንነት ማዕከል የሚያደርግ ነው፡፡ በጤና ተቋማት የልደትና ሞት ምዝገባ እንደሚከናወን ገልጸው፤ ምዝገባው በዲጂታል የተደገፈ መሆኑ የተጣራ የጤና መረጃ ማግኘት ያስችላል ብለዋል፡፡ በሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የሚገኘው የጤና መረጃ ለተወለዱ ህፃናት የሚያስፈልገው የክትባት፣ የሥነ ምግብ አልያም የክትትል ሥርዓቱ ምን መምሰል እንዳለበት ማወቅ እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ለእናቶች የሚያስፈልገውን አገልግሎት መለየት ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ በሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የሞት መንስኤዎችን መለየት የሚያስችል መረጃ እንደሚሰጥ የገለጹት ዶክተር ደረጀ፤ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃፀም መገምገም ያስችላል ብለዋል፡፡ የተደራጀ የዲጂታል ምዝገባ በማካሄድ ተዓማኒ፣ ጥራት ያለውና ጊዜውን የጠበቀ የጤና መረጃ ማግኘት እንደሚያስችልም ተናግረዋል፡፡ የጤና ፕሮግራሞችን ተፈፃሚነት ለመከታተል፣ እቅዶችን ለማውጣት እና ሥራዎችን ለመገምገም አስፈላጊ የመረጃ ምንጭ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የባሕል ፍርድ ቤቶች ስራ መጀመር የማሕበረሰቡ ነባር እሴት እንዲጠናከር ያግዛሉ
Dec 30, 2025 82
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የባሕል ፍርድ ቤቶች እውቅና አግኝተው ስራ መጀመራቸው የማሕበረሰቡ ነባር እሴት እንዲጠናከር እንደሚያግዙ ተመላከተ። የክልሉ የባሕል ፍርድ ቤቶች እውቅና አሰጣጥና ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የክልሉና የፌደራል ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በባሕርዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።   በመርሃ ግብሩ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የባሕል ፍርድ ቤቶች የማሕበረሰቡን ችግር በመፍታት ዘመናትን የተሻገሩ እሴቶች በመሆናቸው እንዲጠናከሩ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሚና በመረዳት ሕጋዊ እውቅና ተሰጥቷቸው እንዲሰሩ ማድረጉ ችግሮችን በጥበብና በብልሃት ለማለፍ የሚያግዝ ነው ብለዋል። የባሕል ፍርድ ቤቶቹ አቅመ ደካማ የሕብረተሰብ ክፍሎች በቅርበት ፍትሕ እንዲያገኙ በማገዝ ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አንስተዋል።   የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች ማሕበረሰቡ የሚያጋጥመውን ችግር የሚፈታበት ከጥንት ጀምሮ ይዞት የመጣ የሽምግልና ስርዓት እንዳለው ገልጸዋል። ይህን አሰራር በባሕል ፍርድ ቤቶች በሕግ አግባብ በማደራጀትና ሕጋዊ እውቅና በመስጠት ወደ ስራ ማስገባት መቻሉ የሚበረታታ ነው ብለዋል። ይሕም መንግስት ችግሮችን በንግግርና በውይይት በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የያዘውን ግብ ለማሳካት እንደሚያግዝ ተናግረዋል። በየአካባቢው ሴቶች፣ ሕጻናትና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን መብትና ጥቅም በማስከበር በኩልም ሚና ይኖራቸዋል ነው ያሉት። የአማራ ክልል መንግስት ወደ ስራ ላስገባቸው የባሕል ፍርድ ቤቶች ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።   የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር ለባሕል ፍርድ ቤቶች መጎልበት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በክልሎች ለባሕል ፍርድ ቤቶች የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። ባሕልን መሰረተ ያደረገ የግጭት አፈታት አሰራርን ለማጎልበት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አለምአንተ አግደው ናቸው።   የክልሉ መንግስት የባሕል ፍርድ ቤቶችን በሕግ አግባብ በማደራጀትና አሰራር በማበጀት ወደ ስራ የሚገቡበትን ሁኔታ ሲያመቻች መቆየቱን አንስተዋል። ሽምግልናን ጨምሮ 15 ሌሎች ማህበራዊ እሴቶች በክልሉ የባሕል ፍርድ ቤቶች እውቅና እንዲሰጣቸው መደረጉን ጠቁመው፤ የባሕል ፍርድ ቤቶቹ ተጠሪነታቸው ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ባሕላዊ ፍርድ ቤቶቹ በአካባቢያቸው ባሕልና ወግ መሰረት ሕብረተሰቡን እንዲያገለግሉ የሚያስችል መሆኑን በማብራራት።
ኢኮኖሚ
በከተማዋ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ ነው
Dec 30, 2025 89
አዳማ ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ መሆናቸውን የከተማዋ አስተዳደር ገለጸ። የዘንድሮውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ሸማቾችንና አምራቾችን ለማገናኘት ያለመ የንግድ ትርዒትና ባዛር በአዳማ ተከፍቷል። የአዳማ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ማቲያስ ሰቦቃ በወቅቱ እንደገለፁት፤ በከተማዋ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ ነው።   ለዚህም የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የግብርናና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶች የዋጋ ንረትና ገበያ ማረጋጋት ላይ አበረታች ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በተለይ ወተት፣ እንቁላል፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የምግብ ዘይትና ሌሎች የፍጆታ እቃዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የንግድ ትርዒትና ባዛሩ ሸማቹን ከአምራቹ ጋር በቀጥታ በማገናኘት በበዓል ምክንያት የግብርና ምርቶችና ሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ እንዳይኖርና ገበያን ለማረጋጋት በማለም የተዘጋጀ መሆኑን አመልክተዋል። በመክፈቻው ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የአዳማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አሸናፊ አጀማ በበኩላቸው፤ በከተማዋ የኑሮ ውድነትን ለመግታት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።   በዚህም አምራቹ በቀጥታ ምርቱን ለሸማቹ እንዲያቀርብ በማድረግ የዋጋ ንረትን በመቀነስ ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እንዲፈፅም እየተደረገ መሆኑን አክለዋል። የከተማ አስተዳደሩ የግብርና ምርቶች የመሸጫ ማዕከላት በመገንባት የተለያዩ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለገበያ እያቀረበ መሆኑን ገልጸው በዚህም ስንዴ፣ ጤፍ፣ ዱቄት፣ የወተት ተዋፅኦን ጨምሮ ዶሮና እንቁላል እንዲሁም ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል ብለዋል። የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስራ አስፈፃሚ አቶ ብዙነህ ግርማ በበኩላቸው፤ኢንቨስትመንት ግሩፑ ገበያን በማረጋጋት ረገድ በቀን ሁለት ሺህ 500 ሊትር ወተትና እንቁላል ለገበያ እያቀረበ መሆኑን ጠቁመዋል።   በተጨማሪም ግሩፑ የገበያ ትስስር በመፍጠር የግብርና ምርቶችና ሸቀጦች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች እንዲደርስ እያደረገ መሆኑን ጠቅሶ ከከተማዋ የንግድ ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ባዛር ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
በክልሉ የቡና ምርትን ከቱሪዝም ጋር በማስተሳሰር በስፋት ለማስተዋወቅ በጋራ መስራት ይገባል 
Dec 30, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቡናን በስፋትና በጥራት በማምረት በዓለም ደረጃ ለማስተዋወቅ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። ቱሪዝም ሚኒስቴር ከታህሳስ 20 ቀን 2018 ጀምሮ ለተከታታይ ስድስት ቀናት "የቡና ቱሪዝምን" በተመለከተ ያዘጋጀውን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የጉብኝት መርሃ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል። ባለሙያዎቹ በሁለተኛው ቀን ውሎአቸው በደቡብ ክልል ጌዲኦ ዞን ይርጋ ጨፌ ገደብ ወረዳ የቡና አመራረት ሂደትን የተመለከተ ጉብኝት አካሂደዋል።   በዚሁ ወቅት የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ ወይኒቱ መላኩ፤ ክልሉ የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ የፖሊሲና ስትራተጂ ማሻሻያዎች ከማድረግ ጀምሮ በርካታ ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በተለይም የክልሉን የቡና ቱሪዝም ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።   ከክልሉ በርካታ ፀጋዎች መካከል አንዱ የሆነው የቡና ልማት ማህበራዊ እሴትን ከማጠናከር ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል። በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ ያለውን የቡና እምቅ አቅም ለመላው ዓለም ለማስተዋወቅ የክልሉ ተወላጆችና የዘርፉ ምሁራን በተለያዩ የዓለም ሀገራት በመዘዋወር የንግድ ትስስር የመፍጠር ስራ እየሰሩ እንደሚገኙ አንስተዋል። የቡና ምርታማነትን አሁን ካለው በተሻለ ለማሳደግ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ አሰራር መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህ ደግሞ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት። በክልሉ ያለውን የቡና ልማት ከቱሪዝም ጋር በማስተሳሰር በስፋት ለማስተዋወቅ በጋራ መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በየአካባቢው ያሉ ሀብቶችን በማልማት የተገኙ ውጤቶች ሁለንተናዊ ዕድገትን ማረጋገጥ እንደሚቻል የሚያሳዩ ናቸው
Dec 30, 2025 49
ሚዛን አማን፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በየአካባቢው ያሉ የተፈጥሮ ሀብቶችን ለይቶ በማልማት የተገኙ ውጤቶች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ማረጋገጥ እንደሚቻል የሚያሳዩ መሆናቸውን የክልል አፈ ጉባኤዎች ገለጹ። የክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች አፈ ጉባኤዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።   አፈ ጉባኤዎቹ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለውንና የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የደንቢ ሐይቅ ሎጅ፣ የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ የግንባታ ሂደት እና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ተመልክተዋል። አስተያየታቸውን የሰጡ አፈ ጉባኤዎች፤ በየአካባቢው ተደብቀው የቆዩ የተፈጥሮ ሀብቶችን ለይቶ በማልማት የተገኙ ውጤቶች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ማረጋገጥ እንደሚቻል ተስፋ የሰነቁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎ እንዳሉት፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ሁለንተናዊ ዕድገትን የሚያረጋግጡ ናቸው።   ከዚህ ቀደም የነበሩ ነገር ግን ያልተጠቀምንባቸውን የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማልማት ወደሚታይ ፍሬ መቀየር መቻሉ ነገን በተሻለ ለውጥ አሻግረን እንድናይ አስችሎናል ብለዋል። እንደ ደንቢ ሰው ሰራሽ ሐይቅ ያሉ ሀብቶችን ከየክልሉ ለይቶ ማየት የሚችል መንግስት በመኖሩ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰው፣ ልማቱን ለማስፋፋት የየአካባቢው አመራር ከህዝብ ጋር ተባብሮ መሥራት አለበት ብለዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ተዘዋውረው ያዩት የተፈጥሮ ሀብት ወደ ኢኮኖሚ ሲቀየር በኢትዮጵያ ዕድገት ላይ ጉልህ ሚና ያበረክታል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር ናቸው።   በገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ኢኒሺዬቲቭ ያለ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የቱሪዝም ኢኮኖሚን ለማጠናከር እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተናግረዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተሠሩና በመሠራት ላይ ያሉ ተፈጥሮን የማልማት ፕሮጀክቶች በቱሪዝም ዘርፍ የገቢ ምንጭና የሥራ ዕድል መፍጠሪያ እየሆኑ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ያለውን ሀብት አውቆ ካለማ በእድገት ወደፊት ከመጡ የዓለም ሀገራት ተርታ የመሰለፍ እድል ይኖረናል የሚል እምነታቸውንም ገልጸዋል። የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አስካለ አልቦሮ በበኩላቸው፤ በሌሎች አካባቢዎች የሌሉ የልማት ተሞክሮዎችን በክልሉ መመልከታቸውን ተናግረዋል።   በተለይ ተፈጥሮን የመጠበቅና የማልማት ልምድን ወደሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ማስፋፋት እንደሚገባ ገልጸው፣ ሕዝብን በማስተባበር የተሻለ ልማት ለማምጣት የተጀመሩ ጥረቶች መጠናከር አለባቸው፤ እኛም የሚጠበቅብንን እንወጣለን ብለዋል።
በተቋማቱ የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የገቢ መጠንን እያሳደጉ ነው
Dec 30, 2025 72
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦በገቢዎችና ጉምሩክ ተቋማት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የታክስና ግብር አሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን የገቢ መጠንን እያሳደጉ መሆናቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ የታክስ ህግ ተገዥነት ላላቸው ግብር ከፋዮች የእውቅና መርሃ ግብር በሀዋሳ ከተማ አካሂዷል።   የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍቃዱ ታደሰ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በገቢዎችና ጉምሩክ ተቋማት የተከናወኑ የለውጥ ስራዎች የግብርና ታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን በየአመቱ የሚሰበሰበውን ገቢ እያሳደጉ ነው፡፡ ተቋማቱን ከ2011 ጀምሮ ሪፎርም በማድረግ የመንግስትን የውስጥ ገቢ ማሳደግ እና ወጪን በራስ አቅም የመሸፈን አቅምን መፍጠር ተችሏል ብለዋል፡፡   በዚህም በ2017 ዓ.ም እንደ ሃገር የተሰበሰበው ገቢ ወደ ትሪሊዮን መግባቱን አስታውሰው በዘንድሮው ዓመትም 1 ነጥብ 28 ትሪሊዮን ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዞ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ባለፉት አምስት ወራት የተሰበሰበው ገቢም የዓመቱን እቅድ ማሳካት የሚያስችል አፈጻጻም የተመዘገበበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የገቢ አቅምን ማሳደግ ትላልቅ ፕሮጀክቶችና የልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ የሃገርን የእድገት ጉዞ እንደሚያፋጥን ያነሱት አቶ ፍቃዱ፣ ገቢን በቀጣይነት ለማሳደግ የአሰራር ስርዓትን ማዘመን፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ማበልጸግና የተቋም ግንባታ ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል። እንደሃገር የህግ ተገዥነት ያላቸውን ግብር ከፋዮች ቁጥር ለማሳደግ የማስተማርና የማበረታታት ስራው እንደሚጠናከር አቶ ፍቃዱ ጠቁመው፣ የዛሬው የእውቅና መርሃ ግብርም የዚሁ አካል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሃብታሙ ታደሰ በበኩላቸው እንዳሉት፤ግብር በሃገር ልማት ላይ ያለውን አበርክቶ ለማስቀጠል በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮች እየተከናወኑ ነው፡፡   በዚህም በቅርንጫፍ ጽህፈቱ ቤቱ የሚሰበሰበው የገቢ መጠን እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው፣ በ2017 በጀት ዓመት ከቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ 5 ነጥብ 36 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል። ገቢው ከቀደመው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ1 ነጥብ 65 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ገልጸው፣ በ2018 ያለፉት አምስት ወራት 2 ነጥብ 84 ቢሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ ከዕቅድ በላይ ለመፈጸም ተችሏል ብለዋል፡፡ የዛሬው መድረክም በቅርንጫፍ ጽህፈቱ ቤቱ ስር ካሉ ግብር ከፋዮች መካከል የተሻለ የህግ ተገዥነት ያላቸውና የሚጠበቅባቸውን ግብር በአግባቡ ለከፈሉ 32 ግብር ከፋዮች እውቅና ለመስጠት የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ እውቅና ከተሰጣቸው ከግብር ከፋዮች ውስጥ ስምንቱ በፕላቲኒየም፣ በወርቅና፣ በብር ደረጃ የተሸለሙ ሲሆን ቀሪዎች በሰርተፊኬት ደረጃ እውቅና የተሰጣቸው መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡   በ2017 በጀት ዓመት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር በመክፈል ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን በመወጣት በፕላቲንየም ደረጃ እውቅና እንደተሰጣቸው የገለጹት ደግሞ የዘቢደር ቢራ አክሲዮን ማህበር ተወካይ አቶ ዮሐንስ ይትባረክ ናቸው፡፡ ለአራት ተከታታይ ዓመታት የፕላቲንየም ደረጃ ተሸላሚ እንደሆኑና በዛሬው መድረክም ልዩ ተሸላሚ መሆናቸውን ጠቅሰው እውቅናው ለተሻለ ሥራ መነሳሳት እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የዲጂታል ልማትና አገልግሎት በኢትዮጵያ መሰረታዊ ለውጥና ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል
Dec 30, 2025 52
ሆሳዕና፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ የዲጂታል ልማትና አገልግሎት በኢትዮጵያ መሰረታዊ ለውጥና ተጨባጭ ውጤት የመጣበት መሆኑን በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ በተለይም በተቋማት አገልግሎት አሰጣጥና በዜጎች የአኗኗር ዘይቤ ላይ የሚታይ ለውጥ የመጣበት በመሆኑ ለቀጣዩ ዕቅድ የላቀ ስኬት መስራት አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል። ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስኬት በመነሳት ተደራሽነትን፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠርንና በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመንን የማጎልበት ዓላማን በመሰነቅ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ መደረጉ ይታወቃል። ኢዜአ ያነጋገራቸው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ሳይንስ መምህርት ፀጋነሽ ሞገስ፤ በኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት በተለይም በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሰረታዊ ለውጥ አምጥቷል ብለዋል።   የአሰራር ፍጥነትን፣ ቁጥጥርንና ተጠያቂነትን እውን በማድረግ ለዜጎች ፍትሃዊ አገልግሎት ለመስጠት በሚደረገው ጥረት የዲጂታል አገልግሎት ትልቁን ድርሻ መያዙን አንስተዋል። የኮደርስ ስልጠና፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ብሔራዊ መታወቂያ የዘርፉን አገልግሎት ይበልጥ እያሳለጡ መሆኑን አንስተው የቴሌብር፣ የባንክና ሌሎችም የተቋማት አገልግሎቶች እመርታዊ ለውጥ አምጥተዋል ብለዋል። የዲጂታል ልማት በድምሩ በኢትዮጵያ መሰረታዊ ለውጥና ተጨባጭ ውጤት የመጣበት መሆኑን ገልጸው፣ ዜጎች በአንድ ቦታ የተለያዩ አገልግሎቶችን በማግኘት እንግልትን እንዳስቀረ ተናግረዋል። ከዚህ በመነሳት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የተያዘውን ሀገራዊ ግብ ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት ማድረግ ይገባል ሲሉ መምህርቷ ተናግረዋል። በዩኒቨርሲቲው የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ መምህር መሳይ አስቻለው፤ በ2025 የዲጂታል ኢትዮጵያ ትግበራ መሰረተ ልማትን ከመዘርጋት ጀምሮ በቴክኖሎጂ የተደራጀ ተቋምና የተሻለ ግንዛቤ ያለው ትውልድ በመገንባት ረገድ ተጨባጭ ስኬት ተመዘግቧል ብለዋል።   የኢትዮጵያን ቀጣይ እጣ ፈንታ ለመወሰን በቴክኖሎጂ ልማት ላይ መስራት ለነገ የማይባል ሥራ መሆኑን አንስተው ለተያዘው እቅድ መሳካት የሁላችንም ጥረትና ትብብር ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በተለይ ዲጂታል 2030 እንደሀገር የተጀመረውን ራዕይ የሚያሳካ መሆኑን ገልጸው፣ ዜጎች በተለይ ወጣቱ በቴክኖሎጂ ብቁ እንዲሆን የተጀመሩ ሥራዎች ለዚህ ስኬት ጉልህ አስተዋጽኦ አላቸው ብለዋል። የኢትዮጵያን እድገትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እውን ለማድረግ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የልማት ግብ ማሳካት እንደሚገባም አጽእኖት ሰጥተዋል። በተለይ ቴክኖሎጂ የሀገርን ኢኮኖሚና ማህበረሰቡን ለማነቃቃት ካለው ጠቀሜታ አንጻር ታይቶ ዘርፉን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ መጠናከር እንዳለበት አመልክተዋል።
የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ መርሃግብር በዲጂታል ስነ ምህዳር ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ያስችላል
Dec 30, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ):- የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ መርሃግብር በዲጂታል ስነ-ምህዳር ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ የሚያስችል ክህሎት እየፈጠረላቸው መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ገለጹ። ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት መሰረተ ልማትና አስቻይ ስርዓት ከመዘርጋት በተጨማሪ የዲጂታል ክህሎት ያለው ማህበረሰብ አስፈላጊ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓም የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ኢኒሼቲቭን ማስጀመራችው ይታወሳል። ኢኒሼቲቩ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስና የኢትዮጵያ መንግስታት የሚተገበር ሲሆን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ 5 ሚሊዮን ወጣቶች በኦንላይን የኮዲንግ ስልጠና የሚወስዱበት ነው። ስልጠናው በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዳሉት የኮደርስ ስልጠና ዘመኑ የሚጠይቀውን የዲጂታል ክህሎት ለማጎልበት መሰረት የሚሆን ነው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽን ሲስተም ተማሪ አርሴማ መንግስቱ የኮደርስ ስልጠና ካለክፍያ የቀረበ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎትን ለመገንባት ዕድል መፍጠሩን ተናግራለች። የኮደርስ ስልጠና ለዲጂታላይዜሽን መፋጠን ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ሰው ስልጠናውን ሊከታተል እንደሚገባ ገልፃለች። በዩኒቨርሲቲው ሌላኛዋ የኢንፎርሜሽን ሲስተም ተማሪ ፅዮን ምስጋናው በበኩሏ የኮደርስ ስልጠና ለሁሉም ሰው በተመቸ አግባብ የተዘጋጀ ነው ብላለች። በኮደርስ ስልጠና ያገኘችው መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ለመደበኛ ትምህርቷ እገዛ እንዳደረገላትም ነው ያስረዳችው። ስልጠናው ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም መመሪያ በሚሆንና ሁሉም ሰው ሊረዳ በሚችለው አግባብ የተዘጋጀ መሆኑን የተናገረችው ደግሞ የኢንፎርሜሽን ሲስተም ተማሪዋ ቤተልሄም ሰለሞን ነች። የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስ ተማሪ ገለታ ካፎ እንዳለው ስልጠናው በኮምፒውተርም ሆነ በስልክ ኦንላይን መከታተል የሚቻል ነው።   ተማሪዎች ስልጠናውን በመከታተል የዲጂታል ክህሎታቸውን ማሳደግ አለባቸው ያለው የዩኒቨርሲቲው የትምህርት አመራርና አስተዳደር ተማሪ ዲቃባ ጎንጂ ነው።      
የጎንደር ከተማ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት በመጪው ጥር ወር ስራ ይጀምራል
Dec 30, 2025 69
ጎንደር፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ የዲጂታል አድራሻ ስርዓትን በመጪው ጥር ወር ስራ ለማስጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ የስማርት ሲቲ ማስተባባሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከጎንደር ከተማ አስተዳደር ጋር ጥቅምት 2018 ዓም ጎንደር ከተማን የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል የፕሮጀክት ስምምነት በተፈረመበት ወቅት ፕሮጀክቱ ጥር ወር 2018 ተጠናቅቆ ወደ ስራ እንደሚገባ መገለጹ ይታወሳል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ የስማርት ሲቲ ማስተባባሪያ ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ይልቃል ሙሉአለም(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤቱ ከስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር በመቀናጀት የዲጂታል አድራሻ ሰርዓት ትግበራን ለማሳካት ሲሰራ ቆይቷል። ስርዓቱ መንግስት ከተሞችን ለማዘመን የጀመራቸውን የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ አጠናክሮ የሚያስቀጥል መሆኑንም ገልጸዋል። ባለፉት ሶስት ወራት ከኢኒስቲትዩቱ ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ የተደገፉ የዲጂታል ዳታዎችን የማሰባሰብና የማደራጀት ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አውስተዋል። በጂፒኤስና በዲጂታል ካርታ የተደራጀው የዲጂታል የአድራሻ ስርዓት በከተማው መሬት ላይ ያሉ ሀብቶችን፤ መሰረተ ልማቶችን ቤቶችንና የዋና ዋና መንገዶች ቋሚ አድራሻዎችን በቀላሉ ለተጠቃሚው አቅጣጫ የሚያመላክት ነው ብለዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂውን ወደ ተግባር ማሸጋገር የሚያስችሉ የሳተላይት ምስልና መረጃ መሰብሰብን ጨምሮ ከ60ሺህ በላይ የመንገድና የትራፊክ እንዲሁም የቦታ መረጃ የማደራጀት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡ ከ74ሺህ በላይ ህንጻዎችና መኖሪያ ቤቶችን ጨምሮ 682 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የዲጂታል የመንገድ ኔትወርክ መረጃዎች ተሰብስበው ወደ ሲስተም መግባታቸውንም አረጋግጠዋል፡፡ ስርዓቱ ለዲጂታል ኢኮኖሚው እድገት መፋጠን፤ ለዘመናዊ ከተማ ግንባታ፤ ለቱሪዝም እንዱስትሪ ማደግ፣ የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመንና የከተማውን ጸጥታና ደህንነት በቴክኖሎጂ ለመቆጣጠር ጠቀሜታ አለው ብለዋል፡፡ ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ፣ የውሃና የቴሌ ኮም የጥገና አገልግሎቶችን ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲያገኙና አገልግሎት የሚሰጡ አካላትም በፍጥነት ደርሰው ምላሽ እንዲሰጡ አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የእሳት አደጋ እና ድንገተኛ የአምቡላንስ እርዳታ አገልግሎቶችን ነዋሪዎች በቀላሉ ማግኘት እንዲችሉ የዲጂታል አድራሻ ስርዓቱ የጎላ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በከተማው የሚገኙ የመንግስት ተቋማት፣ የግል መኖሪያና የንግድ ቤቶችም ዲጂታል መለያ ቁጥር እንደተዘጋጀላቸው ጠቁመው ፕሮጀክቱ ጥር 2018 ዓም ተመርቆ ስራ እንደሚጀመርም ገልጸዋል፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ኢኒሼቲቭ ውጤት የሆነው የዲጂታል አድራሻ ስርዓት የከተማውን እድገትና ልማት የሚጠቁሙ አዳዲስ መረጃዎች በየሦስት ወሩ ወደ ሲስተም የማስገባት ስራ እንደሚቀጥል ታውቀዋል፡፡ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በኢትዮጵያ 100 ከተሞችን ተደራሽ የሚያደርግ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ፕሮጀክት ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ጥቅምት 7/2018 ጎንደር ከተማን የዲጂታል አድራሻ ስርዓቱ ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል ፕሮጀክት የመግባቢያ ሰነድ በተፈረመበት ወቅት መግለጹ ይታወሳል፡፡ በአማራ ክልል ደብረ ብርሃን እና ኮምቦልቻ ከተሞች የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ መሆናቸውንና በደሴና ወልዲያ ከተሞችም ፕሮጀክቱን ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በላቸው ፀሐይ መናገራቸውም እንዲሁ፡፡ በወቅቱ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው እንዳሉት አስተዳደሩ ለፕሮጀክቱ ተፈጻሚነት ከኢንስቲትዩቱ ጋር በቅርበት ይሰራል። ጥር 2018ዓም በከተማው በድምቀት ለሚከበረው የጥምቀት በዓል ቴክኖሎጂውን ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን መናገራቸውም ይታወሳል፡፡
ዲጂታል ሉዓላዊነቷን የጠበቀች፣ በፈጠራና ቴክኖሎጂ የላቀች፣ የበለፀገች ኢትዮጵያ
Dec 30, 2025 118
መንግሥት የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ ወሳኝ ናቸው በማለት ከነደፋቸው ትልሞች መሐከል ዲጂታል ኢትዮጵያን መገንባት ትልቅ ትኩረት የሰጠው ጉዳይ ነው፡፡ የኢትዮጵያን መፃዒ እድል በዛሬና በነገ ትውልድ ፈጠራና ቴክኖሎጂ እድገት ላይ ለመገንባት ያለመው ዲጂታል ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ጥራት ያለው ከዘመኑ ጋር የሚጓዝ አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያስችል ውጤት እየታየበት ይገኛል፡፡ እንደሚታወቀው ይህን ትልም ለማሳካት መንግሥት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ቀርፆ ወደ ስራ ገብቶ ነበር። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በሁሉም መስኮች አስደናቂ ውጤት የተመዘገበበት ሲሆን ስትራቴጂው ስኬታማ ተልዕኮዎቹን አጠናቆ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 አስረክቧል። በዲጂታል 2025 የቴሌኮምን ገበያ በመክፈትና በማስፋት የኢንተርኔት እና ሞባይል አገልግሎት ተደራሽነትን ማሳደግ እንዲቻል አድርጓል። ደህንነቱ የተጠበቀ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (Fayda) ለመላው ኢትየጵያውያን ለማዳረስ የተከናወነው ፕሮጀክት ፣ የኢ-ገቨርናንስ አገልግሎቶች ፣የመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት የዘመነ እና የተቀላጠፈ አገልግሎት በማዳረስ በኩል ትልቅ እመርታ የታየበት ስራ ነው። ሌላው የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ፕሮግራም የዲጂታል ክህሎትን በማስፋፋት በኩል አመርቂ ውጤት የታየበት ነው። ከዚህ በተጨማሪም የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መመስረት፣ የፐብሊክ ኢንፍራስትራክቸር (PKI) መጀመር፣ የኢንተርኔት ፋይበር እና 4G/5G ማስፋፋት፣ ዲጂታል ፋይናንስ ዲጂታል ግብይቶች የመሳሰሉት ሁሉ የዲጂታል 2025 ተልዕኮ ስኬታማነት ማሳያዎች ናቸው። ይህንን መነሻ በማድረግ መንግሥት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ በመቅረፅ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል፡፡ ይህ ስትራቴጂ ዲጂታል ሉዓላዊነቷን የጠበቀች፣ በፈጠራና ቴክኖሎጂ የተመሠረተች ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚያግዝ ስትራቴጂ ሲሆን ስትራቴጂው ቴክኖሎጂን የኑሮ ዘይቤ በማድረግ ሁሉን አቀፍ ብልፅግናን ማረጋገጥ ዓላማው ያደረገ ነው። የስትራቴጂው ምሰሶዎች ተብለው ከተቀመጡት ውስጥ፦ 1) ተደራሽነትን ማስፋት፡ በከተማና በገጠር መካከል ያለውን የዲጂታል ልዩነት በማጥበብ ዜጎች በየትኛውም ስፍራ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ። 2) እኩል ዕድሎችን መፍጠር፡ ዜጎች በዲጂታል ኢኮኖሚው ውስጥ እኩል ተሳትፎና ተጠቃሚነት እንዲኖራቸው ምቹ ሁኔታን ማመቻቸት። 3) መተማመንን መገንባት፡ በተቋማትና በዜጎች መካከል የሳይበር ደህንነትና የውሂብ (Data) ጥበቃን በማረጋገጥ ደህንነቱ የተጠበቀ የዲጂታል ሥርዓት መገንባት ይገኙበታል። እንዲሁም ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ ያላትን ተወዳዳሪነት የምታረጋግጥበትና የመንግሥት አገልግሎቶች በግልጽነት ለዜጎች የሚቀርቡበትን መንገድ የሚያሳልጥ ነው። ከዚህ ባለፈ ስትራቴጂው በግብርናና በጤና፡ ዘመናዊ የዲጂታል መሣሪያዎችን በማካተት ምርታማነትንና የአገልግሎት ጥራትን ማሳደግ፣ በፋይናንስና በትምህርት፡ የፋይናንስ አካታችነትን ማረጋገጥና ለነገው ትውልድ የዲጂታል ፈጠራ አሳቢነትን ማስረጽ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፡ ለዲጂታል ሥራ ፈጣሪዎች ምቹ ምኅዳር በመፍጠር ወጣቶች የፈጠራ አቅማቸውን ወደ ኢኮኖሚ እሴት እንዲቀይሩ ማስቻል የመሳሰሉት ፋይዳዎች ይኖሩታል። የኢትዮጵያን የቱሪስት መስህቦች በዲጂታል አማራጭ ለዓለም በማስተዋወቅ የውጭ ምንዛሪ ገቢን ማሳደግም የዚህ ስትራቴጂ ሌላው ግብ ነው። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሀብት ፈጣሪ አምራች ስታርታፖችና የዲጂታል ክህሎት አቅም በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ ሰፊ የስራ ዕድል መፍጠር ፣የፋይናንስ አካታችነትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማረጋገጥና ዜጎች በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ እንዲችሉ ማድረግ የሚያስችል ተልዕኮዎችም አሉት። የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገለግሎት
ስፖርት
የአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች
Dec 30, 2025 75
የአፍሪካ ዋንጫ በርካታ ክዋክብቶች ደምቀው የታዩበት መድረክ ነው። በሀገራት መካከል ያለው ተቀናቃኝነት፣ አይረሴ ገጠመኞች፣ በደጋፊዎች የተሞሉ ስታዲየሞች እና ሀገራቸውን ለክብር ያበቁ እና ታሪክ የጻፉ ተጫዋቾች በአፍሪካ ዋንጫው ላይ ታይተዋል። የአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎችም የአህጉሪቷ የእግር ኳስ ታሪክ አካል ነው። ካሜሮናዊው ኮከብ ሳሙኤል ኢቶ 18 ጎሎችን በውድድር ላይ በማስቆጠር የቀዳሚነት ስፍራን ይዟል። ኢቶ 10 ጎሎቹን ያስቆጠረው በስድስት የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ ነው። እ.አ.አ በ2006 እና 2008 በተካሄዱ ውድድሮች ላይ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ አጠናቋል። ሁለት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ከሜሮን ጋር አንስቷል።   ኮትዲቯራዊው ላውረን ፖኩ 14 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ተጫዋቹ ግቦቹን ያስቆጠረው በሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ ነው። ፖኩ እ.አ.አ በ1970 በሱዳን አስተናጋጅነት በተካሄደው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ላይ አምስት ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ በርካታ ጎሎችን ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ክብረ ወሰንን ባለቤት ነው። ናይጄሪያው ራሺድ ያኪኒ በ20 የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎች ላይ 13 ግቦችን በማስቆጠር ቀጣዩ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ያኪኒ እ.አ. በ1994 የተካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳ ሲሆን የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪም ነበር።   ግብጻዊው ሀሰን ኤል-ሻዝሊ በስምንት ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ይህም በአንድ ጨዋታ በአማካይ 1 ነጥብ 50 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል እንደ ማለት ነው። ይህም በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ውጤታማው አጥቂዎች ከሚባሉት ተርታ እንዲሰለፍ አድርጎታል። ኤል-ሻዝሊ በሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ፍጻሜ ላይ ሀትሪክ የሰራ ብቸኛው ተጫዋች ነው። ካሜሮናዊው ፓትሪክ ምቦማ፣ ግብጻዊው ሆሳም ሀሰን እና ኮትዲቭራዊው ዲዲየር ድሮግባ በተመሳሳይ 11 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ተከታዩን ደረጃ ይዘዋል’ ፓትሪክ ምቦማ በአፍሪካ ዋንጫ ባደረጋቸው 17 ጨዋታዎች 11 ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል።   ሆሳም ሀሰን እና ዲዲየር ድሮግባ በአፍሪካ ዋንጫ 21 ጨዋታዎችን አድርገው በተመሳሳይ 11 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል። በውድድሩ ላይ ትኩረት ከሚስቡት ጉዳዮች አንዱ ማን ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ያጠናቀቃል? የሚለው ጉዳይ ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ
Dec 30, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዷል። የአዋጁን አስፈላጊነትም የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት እንዲሁም የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች በጋራ ያዘጋጁት ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቧል።   በምክር ቤቱ የሁለቱን ቋሚ ኮሚቲ የውሳኔ ሃሳብ ሪፖርትም የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፈቲያ አህመድ አቅርበዋል፡፡ በሪፖርቱም ረቂቅ አዋጁ የሥርዓተ ምኅዳር ደኅንነትና ዘላቂነትን በማረጋገጥ ጥቅምና የተፈጥሮ አያያዝን ለማሻሻል ወሳኝ መሆኑን በሪፖርታቸው አመላክተዋል። በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ዋጋ ላይ የተፈጠረው ሳይንሳዊ ግንዛቤ ማደግ ለአዋጁ መውጣት መነሻ ምክንያት መሆኑንም አስረድተዋል። የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎቶች ለኢኮኖሚ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ በፖሊሲዎችና በውሳኔ አሰጣጥ ላይ እየተንጸባረቀ የሚገኝ መሆኑም ተገልጿል።   በዚህም የሥርዓተ ምኅዳርን በዘላቂነት ለማስተዳደር የሚያስችል የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ የሕግ ማዕቀፍና የአሰራር ስርዓቶችን መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ በረቂቅ አዋጁ የውሳኔ ሀሳብ ገልጸዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም፤ በረቂቅ አዋጁ ላይ ቢሻሻሉና ቢካተቱ ያሏቸውን ምክረ ሃሳቦች በጥያቄና አስተያየት አቅርበዋል። በቀጣይም የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ የትግበራ አፈፃጸም ውጤታማነትን ለማስጠበቅ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በመጨረሻም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ስብሰባው የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን በመመርመር በአዋጅ ቁጥር 1401/2018 ዓ.ም በአንድ ድምፅ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡
በብሔረሰብ አስተዳደሩ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ሰፊ የውሃ አማራጮችና የልማት እድሎች አግኝተናል--ወጣቶች
Dec 30, 2025 63
ሰቆጣ፤ ታህሳስ 21/2018 (ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የውሃ አማራጮች በመስፋታቸው በመስኖ ልማት በመሰማራት ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን የሰቆጣ ከተማ ወጣቶች ገለፁ። የሰቆጣ ከተማ የ2018 የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ በ04 ቀበሌ ቦሹ ተፋሰስ ላይ ተጀምሯል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ የከርሰ ምድርና ገፀ ምድር የውሃ አማራጮችን በማሳደግ ከ700 በላይ ወጣቶች በንብ ማነብ፣ በከብት ማድለብና በአትክልት ልማት ስራ እንዲሰማሩ ማስቻሉም ተመልክቷል። በወቅቱም ወጣቶቹ፤ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የውሃ አማራጮች በመስፋቱ በመስኖ ልማት ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። በከተማው የ04 ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ወጣት ፋንታው ጌታወይ ለኢዜአ እንደገለፀው በአካባቢያቸው የሚገኘውን ቦሹ ተፋሰስ ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ መልሶ እንዲያገግም አድርገዋል። በእርከን የታገዘው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራው በተፋሰሱ ስር በሚገኙ አካባቢዎች የውሃ ማመንጨት አቅም በመጨመሩ ወጣቶች በመስኖ ልማት እንዲሰማሩ ማስቻሉን ገልጿል። "እኔ ከአሁን ቀደም ምንም ስራ አልነበረኝም" ያለው ወጣት ፋንታው አሁን ላይ ያለሙት ተፋሰሶች የውሃ አማራጮችን በማስፋታቸው በአትክልት ልማት ስራ ላይ ለመሰማራት መቻላቸውን ገልጿል። ሌላው የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት አወጣ ቸኮለ በበኩሉ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ ሽንኩርት፣ ቲማቲምና ድንች እያመረተ መሆኑን ተናግሯል። ያመረተውን ምርትም ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነቱን በማሳደግ ሃብት እያፈራ መሆኑን ገልጿል። በየዓመቱ የሚሰሩ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች በአግባቡ ከተጠበቁ ውጤት እንዳለው በቦሹ ተፋሰስ አረጋግጠናል ያለው ደግሞ ወጣት ፋንታው ፀሃዩ ነው። እያገኘን ያለነውን ጥቅም ዘላቂነት ለማረጋገጥም በዘንድሮው በጋ በሚካሄደው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ግንባር ቀደም ተዋናይ ለመሆን ስራውን መጀመራቸውን አስረድቷል።   የሰቆጣ ከተማ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሚዛን ጌታወይ በከተማው ዙሪያ በሚገኙ ገጠር ቀበሌዎች የለሙ ተፋሰሶች ለወጣቱ የገቢ ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል። የለሙ ተፋሰሶች የአፈር ለምነትን በመጨመር የአርሶ አደሩ ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻላቸውን የገለጹት ደግሞ የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ናቸው። በተጨማሪም የከርሰ ምድርና ገፀ ምድር የውሃ አማራጮችን በማሳደግ ከ700 በላይ ወጣቶች በንብ ማነብ፣ በከብት ማድለብና በአትክልት ልማት ላይ እንዲሰማሩ ማስቻሉን አስረድተዋል።   በብሔረሰብ አስተዳደሩ በተያዘው ዓመት በ366 ተፋሰሶች ላይ የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ማካሄድ መጀመሩን አስረድተዋል። እየተሰሩ ያሉ ተፋሰሶችን ዘላቂነት ለማረጋገጥም የተፋሰሶች ህብረት ስራ ማህበራት በማቋቋም የተጠናከረ ጥበቃና እንክብካቤ እንዲደረግ መሰራቱንም አብራርተዋል።  
በድሬደዋ የተፋሰስ ልማት የአፈርና የውሃ ሀብትን በማልማት የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እያገዘ ነው
Dec 30, 2025 57
ድሬደዋ፣ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ):- በድሬደዋ የተፋሰስ ልማት የአፈርና የውሃ ሀብትን በማልማት የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እያገዘ መሆኑን የአስተዳደሩ ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ። በአስተዳደሩ በዘንድሮ የበጋ ወራት በ5ሺህ 550 ሄክታር የተራቆቱ ተፋሰሶች ላይ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች እንደሚካሄድ ተመላክቷል። በአስተዳደሩ ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና የገጠር መሬት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ አሊይ አህመድ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ባለፉት ዓመታት በተራቆቱ ተፋሰሶቸ ላይ በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ጉዞ ስኬታማ እያደረጉ ናቸው። የተሰሩት የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች ምንጮች እንዲጎለብቱ እና አነስተኛ የመስኖ ልማቶች በአስተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች እንዲስፋፉ አስችለዋል ብለዋል። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎቹ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር እና ለእንሰሳት መኖ ልማት ለማግኘት ማገዛቸውን ጠቁመዋል። ይህም አርሶአደሮች እና አርብቶአደሮች በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን እንዲያረጋግጡ እያስቻለ መሆኑን አቶ አሊይ ተናግረዋል። በተለይም ወጣቶችና ሴቶች የተፋሰስ ልማቱ ላይ በማህበር ተደራጅተው በመንከባከብና በተፋሰስ ልማቱ በተፈጠሩ አዳዲስ የእርሻ መሬቶችን ወደ ልማት በማሸጋገር ተጠቃሚ መሆናቸውን በመግለፅ። እነዚህን ውጤቶች በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል በዘንድሮ የበጋ ወራት 5ሺህ 550 ሄክታር የተራቆቱ ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል ብለዋል። ከተፋሰስ ልማቱ በተጨማሪ ስነ ምህዳሩን የሚያጎለብቱና ለቀጣዩ የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ ስራ መደላድል የሚፈጥሩ ስራዎች እንደሚከናወኑም ገልጸዋል። በዚህ ወር መጨረሻ በሚጀመረው የተፋሰስ ልማት ላይ ከ37ሺህ 550 በላይ የአስተዳደሩ ነዋሪዎች በልማቱ ላይ ይሳተፋሉ ብለዋል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ የገለፁት አርሶአደር ሐሰን ያሶ እና አርሶአደር አብዱላሂ ዩሱፍ በበኩላቸው የተፋሰስ ልማቱ በጎርፍ ይታጠብ የነበረውን ለም አፈር ለልማት በማዋል የተሻለ ምርት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። በተለይም ምንጮች ጎልብተው በመስኖ ልማት መሰማራታቸው የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እንዳስቻላቸው ጠቅሰው ዘንድሮ በሚካሄደው የበጋ ተፋሰስ ልማት ላይ ለመሳተፍ እየተጠባበቁ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ የተገኘውን አበረታች ውጤት ዘላቂ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Dec 29, 2025 133
አርጎባ፤ ታህሳስ 20/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ የተገኘውን አበረታች ውጤት ዘላቂ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የክልሉ የ2018 ዓ.ም የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በደቡብ ወሎ ዞን አርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ዛሬ ተጀምሯል።   በማስጀመሪያው መርሃ ግብር የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ ባለፉት ዓመታት በክልሉ የተከናወነው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘቱን አውስተዋል። ልማቱ የተፈጥሮ ሚዛንን በማስጠበቅ፣ ምርታማነትን በማሳደግ ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ ገቢ ማስገኘት ማስቻሉን ጠቅሰው፤ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ በንብ ማነብና በሌሎችም የተገኘውን አበረታች ውጤት ዘላቂ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል። በውሃ ማሰባሰብ ሥራውም ድርቅን በመቋቋም ለመስኖ ልማት አወንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል። የዘንድሮው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ዛሬ በይፋ መጀመሩን ገልጸው፤ በቀጣይ እስከ አራት ወራት በንቅናቄ ይሰራል ብለዋል። ሰላምና ልማት የማይነጣጠሉ በመሆናቸው ሕብረተሰቡ አንድነቱንና ሰላሙን ጠብቆ ልማቱን ሊያስቀጥል እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ደረጀ ማንደፍሮ፤ የዘንድሮው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ከ9 ሺህ በሚበልጡ ተፋሰሶች ላይ እንደሚከናወን አስታውቀዋል። ሕብረተሰቡን በማሳተፍ 456 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ይከናወናል ብለዋል። ልማቱ ቀጣይነት ሲኖረው ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የደን ሽፋኑን ለመጨመርና ለወጣቱ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል።   ሕብረተሰቡን አስተባብሮ ልማቱን ከማከናወን ባለፈ በለሙ አካባቢዎች አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንዲፈጠር ወደ ሥራ መገባቱን የተናገሩት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሊ መኮንን ናቸው። የልማት ሥራው የአፈር መሸርሸርን በመከላከል የሰብል ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ፣ የእንስሳት መኖ ለማልማትና የአፈር እርጥበትን ለማቆየት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ፋንቱ ተስፋዬ እና በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፤ የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ዋና የትኩረት አጀንዳ
Dec 26, 2025 274
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ነው። መሪ ሀሳቡን ያረቀቀው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የዘንድሮው መሪ ቃል ከአጀንዳ 2063 ጋር የተቆራኘ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። ሁሉም አፍሪካዊ ንጹህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በቂ ውሃ ለመጠጥ፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለሌሎች ፍላጎቶቹ እንዲያገኝ የማድረግ ራዕይን ለማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል።   ህብረቱ የውሃ ደህንነት እንደ አህጉር የተያዙ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማዕቀፎቹ አስቀምጧል። ውሃ እና ንጽህና የኢኮኖሚ እድሎችን በማስፋት፣ የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ፣ የስደቶችና ተፈናቃዮችን ጫና ለማቃለል እንዲሁም ለሰላምና ደህንነት መስፈን አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተመላክቷል። የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ህብረቱ ውሃ እና ንጽህና ለጤና፣ ለኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥና ዘላቂ የአካባቢ ምህዳር ለመፍጠር መሰረት መሆኑን የበለጠ እውቅና እንደተሰጠው አመልክቷል። ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይገበር የውሃ ደህንነትን የማረጋገጥ አላማ ካለው የአፍሪካ የውሃ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው። የዘንድሮው መሪ ቃል የአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጥረቶችን ያስተሳሰረ ድልድይ ሆኗል። በዘላቂ ልማት ግቦች ውስጥ ያለው ግብ ስድስት ከውሃ እና ንጽህና ጋር የተያያዘ ነው። ይህ ግብ እ.አ.አ በ2030 ለሁሌም ዜጋ ደህንነቱ የተረጋገጠ ውሃ አቅርቦትና የንጽህና አጠባበቅን ተደራሽ የማድረግ አላማ አለው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት በፍጥነት መስፋፋትና ውሃ በአግባቡ አለመጠቀም የውሃ ደህንነት እና ዘላቂ አቅርቦት ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። የንጽህና አጠባበቅ የአፍሪካ አንዱ ፈተና ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች መሰረታዊ የሚባል የንጽህና መጠበቂያ መሰረተ ልማቶችን አያገኙም። ይህም እንደ ኮሌራ ላሉ የውሃ ወለድ በሽታዎች መስፋፋት ምክንያት ሆኗል። የተቀናጀ የውሃ አስተዳደር ስርዓት፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ ለዘላቂ መሰረተ ልማት የሚፈሰወን መዋዕለ ንዋይን ማሳደግ፣ ውሃ በድጋሚ አጣርቶ መጠቀም፣ የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ፣ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር እና ለውሃ ደህንነት ትኩረት የሚሰጡ ፖሊሲዎችና ማዕቀፎችን በውጤታማነት መተግበር ያሉትን እድሎች በዘላቂነት ለመፍታትና ፈተናዎችን ለመቅረፍ ያስችላል። ደህንነቱ የተረጋገጠ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ላይ ያለፈውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የቆሸሸ ውሃ በአግባቡ ማከም፣ የንጽህና አጠባበቅ ማስፋትና የግንዛቤ ፈጠራ ስራን በስፋት ማከናወን፣ ማህበረሰብ መር የንጽህና አጠባበቅ ኢኒሼቲቮችን ትግበራ ማስፋት፣ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎችና ሀገር በቀል አቅምን መገንባት ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓትን መፍጠር ያስችላል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና ጤናማ ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸውን ቁልፍ ሚና የሚያሳይ ነው። የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግ መሰረታዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰብ ደህንነትና የተሻለ የኑሮ ዘይቤ፣ ለአካባቢ ጥበቃና ለአፍሪካ ብልጽግና መረጋገጥ ስትራቴካዊ አቅም ናቸው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በሚካሄድበት ወቅት በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም እና 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኞች ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የአፍሪካ ጣሊያን ስብሰባን ለማዘጋጀት ብሄራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 289
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጸንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው-ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
Dec 23, 2025 251
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እና ለረጅም ጊዜ ፀንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኃላፊ አምባሳደር ኮንስታንሲያ አዴሊና ጋስፓራስ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት (ዋይት ሃውስ) በተካሄደ ስነ ስርዓት የአምባሳደር ኮንስታንሲያን ሹመት በይፋ ተቀብለዋል። አምባሳደሯ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ቢሮ ስራቸውን በይፋ ጀምረዋል። ዶናልድ ትራምፕ የአምባሳደር ኮንስታንሲያ የልዑኩ መሪ ሆኖ መመረጥ በጋራ የኢኮኖሚ እድሎች፣ በሉዓላዊ አመራር ሰጪነት እንዲሁም በሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጽኑ አጋርነት የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በአፍሪካ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋትን ማረጋገጥን ዋና ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የአጋርነት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኝ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 305
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 111
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 217
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 448
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 617
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል።   ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ።   ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡   የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።  
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 833
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3205
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 3132
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 4036
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2688
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1720
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7533
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6025
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58982
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53314
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33971
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31503
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27078
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25904
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25454
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25376
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58982
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53314
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33971
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31503
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ወንድማማቾች በአፍሪካ ዋንጫ 
Dec 29, 2025 135
የአፍሪካ ዋንጫ መልከ ብዙ ውድድር ነው። የሀገራት ተቀናቃኝነት፣ ታሪካዊ ገድሎች፣ አይረሴ የተጫዋቾች የግል ብቃት፣ ጨዋታ ወሳኝ ግቦች እና ዋንጫን ከፍ አድርጎ የማንሳት የኩራት እና የሀገር ፍቅር ስሜት መገለጫዎቹ ናቸው። ከሚቆጠሩ ግቦች እና ዋንጫዎች ባለፈ ቤተሰባዊ ገጽታ ያለው ነው። የአፍሪካ ዋንጫ በርካታ ወንድማማች ተጫዋቾች በአንድ ሀገር ማልያ ሲጫወቱ የተመለከትንባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው። በአህጉራዊው መድረክ የ68 ዓመታት ጉዞ አብረው የተጫወቱ ወንድማቾች በዚሁ ጽሁፍ እንመለከታለን። 1. ኢታሎ እና ሉቺያኖ ቫሳሎ (ኢትዮጵያ)   ኢታሎ ቫሳሎ እና ሉቺያኖ ቫሳሎ በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጫወቱ ወንድማማቾች መሆናቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1962 ባዘጋጀችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የቫሳሎ ወንድማማቾች አንድ ላይ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጫውተዋል። ሉቺያኖ በውድድሩ ላይ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ከግብጹ ባደዊ አብድል ፈታህ ጋር በጋራ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ አጠናቋል። ሉቺያኖ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠ ሲሆን ይህም በውድድሩ ታሪክ የኮከብ ተጫዋችነትን ሽልማት ያገኘ የመጀመሪያው ተጫዋች እንዲሆን አስችሎታል። ኢትዮጵያ በወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳቷ የሚታወስ ነው። 2. ሆሳም እና ኢብራሂም ሀሰን (ግብጽ)   ሆሳም ሀሰን እና ኢብራሂም ሀሰን በአፍሪካ ዋንጫው ስኬታማ የሚባሉ ወንድማማች ተጫዋቾች ናቸው። እ.አ.አ በ1986 ግብጽ ያስተናገደችውን 15ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና እ.አ.አ በ1998 በቡርኪናፋሶ የተካሄደውን 21ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ግብጽ ስታነሳ የቡድኑ አባላት ነበሩ። ወንድማማቾቹ የአፍሪካ ዋንጫን ሁለት ጊዜ በማንሳት ባለ ክብረ ወሰን ናቸው። የ59 ዓመቱ ሆሳም ሀሰን በአሁኑ ሰዓት የግብጽ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነው። በተጫዋችነቱ በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የምንጊዜውም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። 3. አልበርት ባዋንጋ እና ሮበርት ካዛዲ (ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ)   ሁለቱ ወንድማማቾች ግብጽ እ.አ.አ በ1974 ባዘጋጀችው ዘጠነኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። በወቅቱ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ዛምቢያን በማሸነፍ ዋንጫውን ስታነሳ የታሪካዊው ድል አካል ነበሩ። 4. አንድሬ ካና ቢይክ እና ፍራንስዋ ኦማም ቢይክ (ካሜሮን)   ሁለቱ ወንድማማቾች በሶስት የአፍሪካ ውድድሮች ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። ተጨዋቾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ በአህጉራዊ መድረክ በጋራ የመሰለፍ እድል ያገኙት እ.አ.አ በ1988 በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው 16ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። እ.አ.አ በ1990 በአልጄሪያ በተካሄደው 17ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ሴኔጋል እ.አ.አ በ1992 ባዘጋጀችው 18ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። ጣልያን እ.አ.አ በ1990 ባዘጋጀችው 14ኛው የዓለም ዋንጫ ከወንድማማቾቹ ታናሹ ፍራንስዋ ኦማም ቢይክ ካሜሮን አርጀንቲናን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ባስቆጠራት ጎል ሁሌም በሀገሬው ሰዎች ሲወሳ ይኖራል። 5. አንድሬ አየው እና ጆርዳን አየው (ጋና)   ጋናውያኑ ወንድማሞች የአፍሪካ ዋንጫ ሲነሳ ሁሌም የሚታወሱ ተጫዋቾች ናቸው። በስድስት የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ አብረው ተሰልፈዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው የሰለፉት ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን እ.አ.አ በ2012 ባዘጋጁት 28ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። የአየው ወንድማማቾች እ.አ.አ በ2015 ኢኳቶሪያል ጊኒ ባዘጋጀችው 30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማንሳት ተቃርበው የነበሩ ቢሆንም በፍጻሜው በኮትዲቭዋር በመለያ ምት ተሸንፈው ህልማቸው ሳይሳካ ቀርቷል። የታዋቂው አፍሪካዊ ተጫዋች አብዲ ፔሌ ልጆች የሆኑት አንድሬ እና ጆርዳን አየው እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለመጨረሻ ጊዜ በጋራ ተሰልፈዋል። ጋና እ.አ.አ በ2008 ባዘጋጀችው 26ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ጋናዊው አጥቂ አሳሞሃ ጊያን እና ታናሽ ወንድሙ ባፎር አንድ ላይ ተጫውተዋል። በተጨማሪም በዛው ውድድር ላይ ጋናውያኑ ወንድማማቾች ሪቻርድ ኪንግስተን እና ላሪያ ጊንግስተን አብረው የመጫወት እድል አግኝተዋል። 6. ኮሎ ቱሬ እና ያያ ቱሬ (ኮትዲቭዋር)   በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ስማቸው በግንባር ቀደምትነት ከሚነሱ ተጫዋቾች መካከል ኮሎ ቱሬ እና ያያ ቱሬ ይጠቀሳሉ። ወንድማማቾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው የተሰለፉት እ.አ.አ በ2006 በግብጽ አስተናጋጅነት በተካሄደው 25ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። በወቅቱ ኮትዲቭዋር ለፍጻሜ ደርሳ በግብጽ ተሸንፋለች። ኢኳቶሪያል ጊኒ እ.አ.አ በ2015 ባዘጋጀችው 30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኮትዲቭዋር ጋናን በማሸነፍ ዋንጫውን ለሁለተኛ ጊዜ ስታነሳ በጋራ የድሉ ተቋዳሽ ሆነዋል። የቱሬ ወንድማማቾች ለስድስት ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫው አብረው ተጫውተዋል። 7. የሞሪታኒያ እና ዛምቢያ ወንድማማች ተጫዋቾች   እ.አ.አ በ2023 ኮትዲቭዋር ባስተናገደችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሪታኒያ ብሄራዊ ቡድን ስብስብ ከሁለት ቤተሰብ በተመሳሳይ ሁለት ወንድማማቾች መሳተፋቸው የተለየ ትኩረት ስቧል። ኑህ መሐመድ አብድ እና ታናሹ ሲዲ መሐመድ አህመድ አብድ በተከላካይ እና አማካይ መስመር ላይ ተሰልፈው ተጫውተዋል። ላሚን ባ እና ኤል ሃጂ ባ ለሞሪታኒያ ብሄራዊ ቡድን በመሰለፍ መጫወት ችለዋል። ዛምቢያዊያኑ ክርስቶፈር እና ፍሊክስ ካቶንጎ እ.አ.አ በ2012 ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን በጣምራ ባዘጋጁት 28ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛምቢያ ኮትዲቭዋር በማሸነፍ የአፍሪካ ዋንጫን ስታነሳ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል።   ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2013 ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይም በጋራ ተሰልፈው ተጫውተዋል። ዛምቢያውያኑ ወንድማማቾች ኬኔት እና ሞርዶን ማሊቶሊ እ.አ.አ በ1994 በቱኒዚያ በተካሄደው 19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ1996 ባዘጋጀችው 20ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አንድ ላይ ተሰልፈዋል። አለን ትራኦሬ እና ኢብራሂማ ትራኦሬ (ቡርኪናፋሶ) በ30ኛው እና 31ኛው የአፍሪካ ፣ ሳምቡ ያታባሬ እና ሙስጠፋ ያታባሬ (ማሊ) በተመሳሳይ በ30ኛው እና 31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ፒተር ንዶልቩ እና አዳም ንዶልቩ (ዚምባቡዌ) በ24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ሳሉ፣ ባቺሩ እና ታጁ (ቶጎ) በ22ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ቾሞጎ ኦማር እና ሴዲያት ኦማር (ቤኒን) በ24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ መሐመድ እና ሙሳ ካሎን (ሴራሊዮን) በ20ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ሳሚር ሳሊሚና አዴል ሳሊሚ (ቱኒዚያ) በ19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አብረው የተሰለፉ ተጫዋቾች ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫ ከተሰለፉ ወንድማማቾች መካከል ስድስቱ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳታቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታውቋል።
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር  ተሻጋሪ ወዳጅነት 
Dec 16, 2025 572
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።  
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም