ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ሲዳማ ቡና ሃዋሳ ከተማን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ
Feb 28, 2026 42
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐ-ግብር ሲዳማ ቡና ሃዋሳ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብርሃኑ በቀለ እና መስፍን ታፈሰ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ተባረክ ሄፋሞ ለሃዋሳ ከተማ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሲዳማ ቡና በ39 ነጥብ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል። በሊጉ 10ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሃዋሳ ከተማ በ36 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ጨዋታውን ተከትሎ 21ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ22ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከየካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
ፈተናዋን የተሻገረች ተስፈኛ ሴት ማፍሪያ ማዕከል የሆነው - ለነገዋ
Feb 28, 2026 51
ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል በተለያየ የሙያ መስክ ያሰለጠናቸውን የአራተኛ ዙር ሰልጣኞች አስመርቋል። በመርሃግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ሌሎች የከተማ አስተዳደሩ አመራር አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ወጣት ቤተልሄም በቀለ የአባቷ ህይወት ማለፍ እንዲሁም የእናቷ አቅም ማጣት ከኑሮ ጫና ጋር ተደማምሮ ትምህርቷን ጨርሳ ወደ ስራ እንድትሰማራ አላስቻላትም። ግራ በገባት ጊዜ መንገዷን ሊያቀና ነገዋን ሊያሰምር የሚችለውን መስመር ስትሻ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከልን አገኘች። በማዕከሉ በፋሽን ዲዛይን በመሰልጠንም በዛሬው እለት የእጅ ስራዋ በሆነው ጥበብ ደምቃ ለምረቃ በቅታለች። በቀሰመችው እውቀትና ክህሎት ተግታ ነገ ላይ የተሻለ ሆኖ መገኘትን እንደምትፈልግና ለዚህም ውጥን መሰነቋን ገልጻ፤ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ያሉ ሴቶች ነገ የተሻለ አለና በርቱ ተስፋን ሰንቃችሁ ተጓዙ የሚል ምክርን ለግሳለች። በዛሬው እለት ስልጠናቸውን ካጠናቀቁ ሴቶች መካከል አስቴር አለማየሁ በበኩሏ በማዕከሉ የሙያ ባለቤት ሆኛለሁ ብላለች፡፡ በሰለጠነችበት ዘርፍ ውጤታማ ለመሆን እንደምትፈልግ በመግለጽ፤ ለዚህም ተስፋ ባለመቁረጥ በቀጣይ ጠንክራ እንደምትሰራ ተናግራለች። ከዚህ ቀደም በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋ ለዚህ መድረሷን የምትገልፀው ደግሞ ሌላዋ በማዕከሉ ሰልጥና የሙያ ባለቤት የሆነችው ነፃነት እጅጉ ነች፡፡ በማዕከሉ እውቀትና ክህሎት ከመገብየቷ ባለፈ ስራ በማግኘቷ ደስተኛ መሆኗንና በቀጣይም በርትታ በመስራት ለሌሎች መትረፍን የረዳትን ማህበረሰብን ማገልገል እንደምትሻም ተናግራለች። የለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ከተማ አስተዳደሩ የሚሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች ማሳያ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ሂርጳሳ ጫላ(ዶ/ር) ናቸው። ማዕከሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ስነ ልቦናዊ ድጋፍ የሚሹ ሴቶችን በማሰልጠን ወደ ስራ እንዲገቡ ማስቻሉን ጠቁመው፤ በአራተኛው ዙር ስልጠና የወሰዱ 909 ሴቶች ለምረቃ መብቃታቸውን ተናግረዋል። ሰልጣኞች የንድፈ ሃሳብና የክህሎት ስልጠና አጠናቀው የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ወስደው 97 ነጥብ 5 በመቶ በላይ ማለፋቸውንም ገልጸዋል። እስካሁኑ ባለው የስልጠና ሂደትም 2ሺህ 401 ሴቶችን ማሰልጠኑንና ሰልጣኞች የተሃድሶና የሙያ ስልጠና ማግኘታቸውን ገልፀዋል። ማዕከሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ስነልቦናዊ ድጋፍ ለሚሹ ሴቶች የሚሰጠውን ስልጠና ለማስፋት ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ቦርንማውዝ እና ሰንደርላንድ ነጥብ ተጋሩ
Feb 28, 2026 50
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ቦርንማውዝ እና ሰንደርላንድ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በቫይታሊቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኤሊዘር ማዬንዳ በ18ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ ሰንደርላንድ መሪ ሆኗል። ከእረፍት መልስ ኢቫኒልሰን በ64ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል ቦርንማውዝን አቻ አድርጋለች። ባለሜዳው ቦርንማውዝ በኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢወስድም ቡድኖቹ ተመጣጣኝ ሊባል በሚችል ሁኔታ ኢላማቸውን የጠበቁ የግብ ሙከራዎችን አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ቦርንማውዝ በ39 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። ቦርንማውዝ ባለፉት ሁለት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። ሰንደርላንድ በ37 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ቡድኑ ባለፉት አራት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም።
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 27 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ሥራ ገብተዋል
Feb 28, 2026 80
ጎንደር፤ የካቲት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 27 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ሥራ እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን የዞኑ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ። አሀዱ ቢዝነስ ግሩፕ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ በ112 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያቋቋመው የቅባት እህሎች ማበጠሪያና ማቀናበሪያ ፋብሪካ ተመርቋል። በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ የመምሪያው ሃላፊ አቶ የአብስራ እሸቴ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በዞኑ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ችግር በመፍታት በሙሉ አቅማቸው ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩ እየተደረገ ነው። ንቅናቄውን ተከትሎ 27 ኢንዱስትሪዎች ወደማምረት ሥራ መግባታቸውን ገልጸው ባለፉት ስባት ወራት ብቻ በምግብ ዘይት፣ በጨርቃ ጨርቅና በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ሰባት አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል። አምራች ኢንዱስትሪዎቹ የማምረቻ ማሽኖችን ከውጪ ከቀረጥ ነጻ እንዲያስገቡ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር ጀምሮ ከ189 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ከፋይናንስ ተቋማት ብድር እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመዋል። ወደ ምርት ሥራ የገቡት አምራች ኢንዱስሪዎችም ከ300 በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የሥራ እድል መፍጠራቸውንም ነው አቶ የአብስራ የገለጹት። በዓመቱ እስካሁን ድረስ 7 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ካፒታል ላስመዘገቡ 76 ባለሀብቶችም የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል። ፈቃድ የተሰጣቸው ኢንቨስትመንቶች ወደማመረት ሲሸጋገሩ ከ10 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩም ገልጸዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ በበኩላቸው እንዳሉት በዞኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ በመደረጉ ለበርካታ ወገኖች የሥራ እድል እየተፈጠረ ነወ። ዞኑ በአግሮ ኢንዱስትሪ ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች በጥሬ እቃነት ሊውሉ የሚችሉ የቅባትና የጥራጥሬ ሰብሎች በስፋት የሚመረትበት አካባቢ መሆኑንም አስረድተዋል። የአሀዱ ቢዝነስ ግሩፕ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ብርሀኑ ባዩህ ፋብሪካው በ112 ሚሊዮን ብር ካፒታል መቋቋሙን ገልጸዋል። በቀን 800 ኩንታል ሰሊጥና አኩሪ አተር አቀናብሮና አሽጎ ለዓለም ገበያ የማቅረብ አቅም እንዳለውም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በፋብሪካው ለ20 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው፣ በቀጣይም የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ በመክፈት ከውጪ የሚገባን ዘይት ለመተካት መታቀዱን ተናግረዋል። ፋብሪካው በዓመት ከ290 ሺህ ኩንታል በላይ ሰሊጥና አኩሪ አተር በግብአትነት እንደሚጠቀም ገልጸው፣ ይህም ለአምራች አርሶ አደሮች ሰፊው የገበያ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል ። በፋብሪካው የምረቃ ሥነስርዓት ላይ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው ባለሀብቶች ተገኝተዋል።
በአማራ ክልል ህገ-ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከል የሚደረገው የተቀናጀ ጥረት ውጤት እያስገኘ ነው
Feb 28, 2026 54
ባህርዳር፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ህገ-ወጥ ንግድንና ኮንትሮባንድን በተቀናጀ አግባብ በመከላከል የህግ ተገዥነትን ለማረጋገጥ እየተከናወነ ያለው ስራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ የምርትና ግብይት፣ የገበያ አረጋጊ፣ የፀረ-ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ጥምር ግብረ-ኃይል፤ የወንጀል ጉዳዮች ቴክኒክ ኮሚቴ የሥራ አፈጻጸም ግምገማውን ዛሬ በባህርዳር ከተማ አካሂዷል። በቢሮው የኢኮኖሚ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክተር ሙሉጌታ አሻግሬ እንደገለጹት፤ የቴክኒክ ኮሚቴው 13 ተቋማትን በማቀፍ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል በቅንጅት እየሰራ ይገኛል። በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት በህገ-ወጥ ተግባር ተሰማርተው በተገኙ 190ሺህ 150 የንግድ ድርጅቶችና ማህበራት ላይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ፣ የሥራ እገዳና የንግድ ፈቃድ ስረዛ እርምጃዎች ተወስደዋል ብለዋል። ምርቶችን በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ውስጥ ሲያስገቡና ወደ ውጭ ሲያስወጡ ተይዘው በተገኙ 128 ነጋዴዎች ላይ ደግሞ እስከ 12 ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት ተላልፏል ነው ያሉት። ይህ ውጤት ሊመዘገብ የቻለው በተቋማቱ መካከል ያለውን የመረጃ ልውውጥና የጋራ ቁጥጥር በማጠናከር መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢብራሂም መሀመድ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጤናማ ለማድረግ ህገ-ወጥ የኬላ ቀረጥ፣ የኮንትሮባንድ ዝውውርና የነዳጅ ስርጭት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፈው ሳምንት ብቻ 34 ሰዎች ነዳጅን ከማደያ አውጥተው በህገ-ወጥ መንገድ ሲያጓጉዙ እጅ ከፈንጅ መያዛቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደጀን ወዳጅ፤ የነዳጅ፣ የጦር መሳሪያ፣ የመድኃኒትና የምግብ ነክ ምርቶች ህገ-ወጥ ዝውውርን ለማስቆም የተከናወነው ስራ አበረታች መሆኑንና በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ፖለቲካ
ፓርቲዎች ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ምርጫን በሀሳብ የበላይነት ለማሸነፍ የጀመሩት ጥረት መጠናከር አለበት −ምሁራን
Feb 28, 2026 78
ዲላ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ) ፡-የፖለቲካ ፓርቲዎች ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ በማቅረብና በማስተዋወቅ ምርጫን በሀሳብ የበላይነት ለማሸነፍ የጀመሩት ጥረት የሚበረታታና መጠናከር ያለበት ነው ሲሉ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ምርጫ ዴሞክራሲ የሚገነባበት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መስፈርት መሆኑን ያነሱት ምሁራኑ ውጤታማ ምርጫ በማካሄድ የሀገርን መልካም ስም ማስቀጠል እንደሚገባም ተናግረዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ ዓለሙ (ዶ/ር)፣ የውስጥ አቅምን በመጠቀም ውጤታማ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ምቹ የፖለቲከ ምህዳር በመንግስት ስለመፈጠሩ ጅማሬው እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲዎች ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ በማቅረብና በማስተዋወቅ ምርጫን በሃሳብ የበላይነት ለማሸነፍ የጀመሩት ጥረት የሚበረታታ መሆኑን አንስተው ይህም መጠናከር እንዳለበት አመልክተዋል። ምርጫ ዴሞክራሲን ከመገንባት ባለፈ የህዝብ ድምጽ እንዲደመጥ ያደረጋል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ በሰከነና የምርጫ ህጉን በተከተለ መልኩ የሚደረግ የሀሳብ ሙግትና ፉክክር የተሻለ የፖለቲካ ስርዓት በመገንባት ሀገርን ያጸናል ብለዋል። በመሆኑም ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እና መራጩ ህዝብ የሃሳብ የበላይነትን ለድርድር ማቅረብ የለባቸውም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ምርጫ የዲሞክራሲ ልምድ የሚገነባበት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መስፈርት መሆኑን ያነሱት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የትምህርት ዘርፍ መምህርና ተመራማሪ ደረጄ ክፍሌ (ዶ/ር) ናቸው። በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደውን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ በማድረግ የሃገርን መልካም ስም ለመገንባት ሁሉም የምርጫው ተዋናዮች በሃላፊነት ስሜት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ማኒፌስቶና ያሏቸውን አማራጮች ለህዝብ ለማስተዋወቅ የጀመሯቸውን ጥረቶች አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል። በተለይ ፓርቲዎች በሀሳብ የበላይነት ልቆ ለመውጣት ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው ተናግረው በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ከግጭት ቀስቃሽ ንግግርና ተግባር መቆጠብ አለባቸው ብለዋል። በሀሳብ የበላይነት ምርጫን ለማሸነፍ የሚደረጉ ጥረቶች ዴሞክራሲ እንዲያብብ ሚናው የጎላ በመሆኑ ፓርቲዎችና አባላቶቻቸው በዚህ መልክ የጀመሩትን ጥረት ማጠናከር እንዳለባቸው አመልክተዋል።
የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት መሳተፍ ይጠበቅባቸዋል
Feb 28, 2026 89
ሰመራ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት መሳተፍ እንደሚጠበቅባቸው የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ገለፀ። ፌዴሬሽኑ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ታዛቢዎችን ለማሰማራት በአፋር ክልል ክላስተር ደረጃ የታዛቢዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናውን ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር ገነት ስዩም እንደተናገሩት ሴቶች በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ ሁኖ እንዲጠናቀቅ ሀላፊነታቸው መወጣት አለባቸው። ሴቷ ለመመረጥም ይሁን ለመምረጥ እንዲሁም በታዛቢነት ተሳትፎዋን ማሳደግ እንድትችል የአሰልጣኞች ስልጠናው ጉልህ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል። ላለፉት ዓመታት ምርጫዎችን በመታዘብና ግንዛቤ በመስጠት የተሳተፈው ፌዴሬሽኑ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት በማሳደግ ረገድም ሰፋፊ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ገልፀዋል። የመራጮችን ግንዛቤ ከማሳደግ አንጻር በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በተለያዩ አማራጮች በመጠቀም የማህበረሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ተናግረዋል። የአፋር ክልል ሴቶች ፌዴሬሽን ዳይሬክተር ፋጡማ ሐንፈሬ በበኩላቸው እየተሰጠ ያለው የአሰልጣኞች ስልጠና ቀጣዩ ምርጫ ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚያግዝ ነው።
ምርጫው ለዴሞክራሲ ስርዓት መጎልበትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ጥሩ መሰረት እንዲያኖር የፖለቲካ ፓርቲዎች መስራት ይገባቸዋል
Feb 28, 2026 76
መቱ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጎልበትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ጥሩ መሰረት እንዲያኖር የፖለቲካ ፓርቲዎች መስራት እንደሚገባቸው ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የምርጫ ሂደቱም ነፃ፣ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፓርቲዎች የምርጫ ህጉን አክብረው እንዲሰሩ አስገንዝቧል። አጠቃላይ የምርጫ ሂደቱንና የፓርቲዎችን ሃላፊነት በተመለከተ ኢዜአ በመቱ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራንን አነጋግሯል። በዩኒቨርሲቲው የሕግ ትምህርት ቤት ዲን ዩሱፍ ጋዛሊ፤ የምርጫ ዴሞክራሲያዊነት መለኪያው ሂደቱና የፓርቲዎች ሰላማዊና ደሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በቅድመ ምርጫ ፓርቲዎች የምርጫ ስነ ምግባር ደንቡን በማክበር የመወዳደሪያ ሐሳባቸውን ለሕዝብ በመሸጥ ተቀባይነት ለማግኘት መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። ፓርቲዎች የሃሳብና የፖሊሲ ክርክር ላይ ማተኮር እንዳለባቸውም ተናግረዋል። በምርጫው መሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብትና የዜግነት ኃላፊነት በመሆኑ በሂደቱ ለሀገር ሕልውናና ቀጣይነት ቅድሚያ ሰጥተው መስራት ግደታ እንዳለባቸውም አንስተዋል። በመሆኑም የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጎልበትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ጥሩ መሰረት አኑሮ እንዲያልፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች መስራት ይገባቸዋል ነው ያሉት። በዩኒቨርሲቲው የሥነ-ባሕርይ እና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ መምህር ወንዱ መብራቴ፤ በምርጫው የሚፎካከሩና የሚሳተፉ ሁሉ ከምንም በላይ የሀገርን ሰላምና ህልውና ጉዳይ ቅድሚያ መስጠት ግደታ አለባቸው ብለዋል። በምርጫው ሂደት ፓርቲዎች በሀሳብ የበላይነት ለመወዳደር ዝግጁ ሆነው አሸናፊ ሃሳብ ይዘው ሊመጡ እንደሚገባም ገልጸዋል። በመሆኑም ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲካሄድ የሚፎካከሩ ፓርቲዎችና ደጋፊዎች የየበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ድምጽ አሸናፊ የሚሆንበት ለማድረግ በትኩረት እየሰራን ነው - ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች
Feb 28, 2026 136
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ድምጽ አሸናፊ የሚሆንበትና የሕዝብ ፍላጎት የሚንጸባረቅበት እንዲሆን በትኩረት እየሰሩ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገው የጊዜ ሰሌዳ ያሳያል። ቦርዱ ምርጫውን ማካሄድ የሚያስችሉ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ሲሆን የመራጮች ምዝገባም ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ያካሂዳል። ፓርቲዎችም ዕጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን ምርጫ አስፈጻሚዎች የአሰልጣኞች ሥልጠናም በቦርዱ በኩል እየተሰጠ ይገኛል። በቅርቡ ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕጩዎች የሥነ ምግባር ደንብም አዘጋጅቷል። ምርጫውን ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ተዓማኒ ለማድረግ ያለመውን የሥነ ምግባር ደንብ ፓርቲዎች ፈርመውታል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምርጫው የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጥበት እንዲሆን እየሰሩ ነው። የአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሊቀ መንበር ተስፋሁን ዓለምነህ፤ ፓርቲው በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በርካታ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ምርጫው የሕዝብ ፍላጎት የሚንጸባረቅበት፤ ሕዝብ አሸናፊ የሚሆንበት አካሄድ ተከትለን በምርጫው ለመሳተፍ ዝግጁ ነን ብለዋል። ምርጫው በሂደቱም፣ በውጤቱም ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ተዓማኒ መሆን ይኖርበታል ያሉት አቶ ተስፋሁን በዚህ ረገድ ፓርቲያቸው የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው በምርጫው መወዳደር የሚያስችለውንና አማራጭ ሀሳብ የያዘውን ፕሮግራም መቅረጹን ጠቅሰው በምርጫው ለዲሞክራሲ ሥርዓት መጎልበት የበኩሉን አሻራ ለማሳረፍ ተግቶ ይሰራል ብለዋል። የሲዳማ አንድነት ፓርቲ ሊቀ-መንበር ለማ ኦያቶ በበኩላቸው፤ ፓርቲው ዕጩዎቹን ማስመዝገቡንና ለፓርቲው አባላት የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠቱን አስታውቀዋል። ምርጫው ሠላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ ፓርቲው የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አስረድተዋል። የወለኔ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር ፈይሰል አብዲላዚዝ እንደገለጹት፤ ለምርጫው ስኬታማነት የቦርዱን እንዲሁም የሀገሪቱን ሕግ አክብሮ መንቀሳቀስ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ፓርቲው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በቅርቡ ይፋ ያደረገውን የዕጩዎች የሥነ ምግባር ደንብ መፈረሙን ጨምረው ጠቁመዋል። ተፎካካሪ ፓርቲዎች መሰል የሥነ ምግባር መርሆዎችን በመከተልና በመተግበር ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክራቸውን የሀገርን ልማትና የህዝብን አብሮነት ማዕከል ባደረገ መልኩ ማካሄድ አለባቸው
Feb 27, 2026 150
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የርዕዮተዓለም የምርጫ ክርክራቸውን የሀገርን ልማትና ዕድገት፣ የህዝብን አብሮነት እና መስተጋብር ማዕከል ባደረገ መልኩ ማካሄድ እንደሚኖርባቸው አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በምርጫው የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን አማራጮች የመወዳደሪያ ምልክትና ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም በምርጫው ድምጽ መስጠት የሚችሉበትን ካርድ ለመውሰድና ይበጀኛል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እየተጠባበቁ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችም፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለህዝብ የሚያቀርቧቸው የምርጫ ቅስቀሳና ክርክሮች ከስሜት ይልቅ ዕውቀትና ምክንያታዊነትን ያስቀደሙ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኅን በኩል በክርክሮች ላይ የሚያቀርቧቸው አማራጭ የፖሊሲ ሀሳቦችና በቀጣይም የምረጡኝ ቅስቀሳዎች ዜጎች ይበጀኛል ለሚሉት ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል። አቶ ከድር ሰኢድ እንደገለጹት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ የክርክር መድረኮቹ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማትና ዕድገት አዋጭ የሆኑ ሃሳቦችን ያነገቡ የፖለቲካ ድርጅቶችን ለይቶ ድምጽ ለመስጠት ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። በዘንድሮው ምርጫ ላይ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ክርክር ወቅትም ህዝብን የሚመጥን በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ሃሳቦችን ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ውበት ደጉ በበኩሏ፤ ምርጫ ዜጎች ይበጀኛል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ የሚሰጡበት የአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት መገለጫ ነው ብላለች። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክርም የሀገርን ልማትና ዕድገት፣ የህዝብን አብሮነትና ዘላቂ ሰላም ግንባታ ማዕከል ማድረግ እንደሚኖርበት ገልጸዋል። ህዝቡም በመገናኛ ብዙሃን የሚተላለፉ የምርጫ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎችን ክርክርን በመከታተል ሀሳባቸውን ከብሄራዊ ጥቅም አኳያ መፈተሽ እንዳለበት አመልክተው፤ ለሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊነት ገንቢ ሚና መወጣት እንዳለበት ተናግረዋል። አቶ አማን ማሞ በበኩላቸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ የህዝብን አንድነትና ሰላም ባከበረና በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ መሆን አለበት ብለዋል። ምርጫ የጠንካራ መንግስት ምስረታ፣ የሰላማዊ ፉክክርና የዴሞክራሲ ሥርዓት መገለጫ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ትዕግስት ማሞ ናቸው። በዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ክርክር ወቅት ዕውቀትና የሀገርን ቀጣይነት የሚያስቀድሙ ሃሳቦችን ለህዝቡ በመሸጥ ለምርጫው ዴሞክራሲያዊነት በኃላፊነት መንፈስ መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ገልጸዋል። መራጩ ህዝብም ለሀገርና ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይሰራል ይበጃል ለሚለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት የሚችሉት የምርጫ ክርክሩንና የቅስቀሳ መርሃ ግብሩን ሲከታተሉ መሆኑን ነው የተናገሩት።
በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Feb 27, 2026 104
ሆሳዕና፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች መመዝገባቸውን የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ባደረጋቸው ጥረቶች የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ያስቀጥላል በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲ ምህዳርን በማጠናከር አዲሷን ኢትዮጵያን ለመገንባት ሚናው የጎላ መሆኑም ተመላክቷል። ብልጽግና ፓርቲ የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን (የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ለህዝብና ለአባላቱ አስተዋውቋል፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ በዚህ ወቅት እንዳሉት ብልጽግና ፓርቲ በድህነት ቅነሳ ላይ ባከናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል። ፓርቲው የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሀሳቦችን በማቅረብና ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ጭምር በትብብር በመስራት ስኬት እያስመዘገበ መሆኑንም አስታውሰዋል፡፡ በዞኑ በሰላም ግንባታ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በጤናና በትምህርት ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ ወጤት እየተመዘገበ ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከድህነት በመውጣት በምግብ ራስን ለመቻል በተተገበሩ የሌማት ትሩፋት መርሀግብርና ሌሎች ኢኒሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት መምጣቱንም ጠቁመዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በፓርቲው መሪነት በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ የልማት ሥራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ነው ያስታወቁት። በዞኑ በልማትና በመልካም አስተዳደር በተሰሩ ሥራዎች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የፓርቲው አመራሮችና አባላት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የሀዲያ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ግዛው በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግሥት የፖለቲካ ስልጣን ቅቡልነት በህዝብ ድምፅ ብቻ እንዲወሰን ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በሀገሪቱ የተጀመረውን የዴሞክራሲ ምህዳር በማጠናከር ለአዲሷ ኢትዮጵያ ግንባታ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የፓርቲው አባላት ተሳትፈዋል፡፡
ምርጫው ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው- ፓርቲዎች
Feb 27, 2026 106
ደሴ ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድና ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክሮች ለሀገርና ህዝብ በሚጠቅሙ የፖሊሲ አጀንዳዎች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል በአማራ ክልል ደሴ ከተማና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በደሴ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂደዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢና በኢዜማ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ሻምበል ደምሌ ተረፈ፤ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት መዳበርና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ምርጫ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ የጋራ ምክር ቤቱ የዘንድሮው ምርጫ በሃሳብ የበላይነት በመፎካከር ሀገርን አሸናፊ የሚያደርግ እንዲሆን ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድና ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው ሲሉም ተናግረዋል። የዛሬው ውይይት ዋነኛ ዓላማም በምርጫው ሂደት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በጋራ በመፍታት ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ማካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢና በብልጽግና ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁ፤ ለምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የጋራ ምክር ቤቱ አባላት በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። ለምርጫው ተወዳዳሪ እጩዎችንና ታዛቢዎችን መመልመላቸውን ጠቁመው በቅስቀሳ ወቅት ከጠብ አጫሪነትና ጥላቻ ንግግሮች በመራቅ መራጩ የጠራ ግንዛቤ አግኝቶ እንዲወስን ማድረግ የሁላችንም ሃላፊነት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባልና የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ተወካይ አቶ ያለው አሸብር፤ በሀገር ዘላቂ ሰላም፣ ጥቅምና ልማት ፓርቲያችን አይደራደርም ብለዋል። በወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ መሀመድ የሱፍ፤ በቅደመ ምርጫ፣ በምርጫና በድህረ ምርጫ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማስተካከል የዛሬው ምክክር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በሁሉም ፓርቲዎች ዘንድ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማስተካከል የተሳካ ምርጫ ለማካሄድ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።
ፖለቲካ
ፓርቲዎች ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ምርጫን በሀሳብ የበላይነት ለማሸነፍ የጀመሩት ጥረት መጠናከር አለበት −ምሁራን
Feb 28, 2026 78
ዲላ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ) ፡-የፖለቲካ ፓርቲዎች ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ በማቅረብና በማስተዋወቅ ምርጫን በሀሳብ የበላይነት ለማሸነፍ የጀመሩት ጥረት የሚበረታታና መጠናከር ያለበት ነው ሲሉ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ምርጫ ዴሞክራሲ የሚገነባበት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መስፈርት መሆኑን ያነሱት ምሁራኑ ውጤታማ ምርጫ በማካሄድ የሀገርን መልካም ስም ማስቀጠል እንደሚገባም ተናግረዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ ዓለሙ (ዶ/ር)፣ የውስጥ አቅምን በመጠቀም ውጤታማ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ምቹ የፖለቲከ ምህዳር በመንግስት ስለመፈጠሩ ጅማሬው እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲዎች ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ በማቅረብና በማስተዋወቅ ምርጫን በሃሳብ የበላይነት ለማሸነፍ የጀመሩት ጥረት የሚበረታታ መሆኑን አንስተው ይህም መጠናከር እንዳለበት አመልክተዋል። ምርጫ ዴሞክራሲን ከመገንባት ባለፈ የህዝብ ድምጽ እንዲደመጥ ያደረጋል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ በሰከነና የምርጫ ህጉን በተከተለ መልኩ የሚደረግ የሀሳብ ሙግትና ፉክክር የተሻለ የፖለቲካ ስርዓት በመገንባት ሀገርን ያጸናል ብለዋል። በመሆኑም ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እና መራጩ ህዝብ የሃሳብ የበላይነትን ለድርድር ማቅረብ የለባቸውም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ምርጫ የዲሞክራሲ ልምድ የሚገነባበት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መስፈርት መሆኑን ያነሱት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የትምህርት ዘርፍ መምህርና ተመራማሪ ደረጄ ክፍሌ (ዶ/ር) ናቸው። በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደውን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ በማድረግ የሃገርን መልካም ስም ለመገንባት ሁሉም የምርጫው ተዋናዮች በሃላፊነት ስሜት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ማኒፌስቶና ያሏቸውን አማራጮች ለህዝብ ለማስተዋወቅ የጀመሯቸውን ጥረቶች አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል። በተለይ ፓርቲዎች በሀሳብ የበላይነት ልቆ ለመውጣት ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው ተናግረው በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ከግጭት ቀስቃሽ ንግግርና ተግባር መቆጠብ አለባቸው ብለዋል። በሀሳብ የበላይነት ምርጫን ለማሸነፍ የሚደረጉ ጥረቶች ዴሞክራሲ እንዲያብብ ሚናው የጎላ በመሆኑ ፓርቲዎችና አባላቶቻቸው በዚህ መልክ የጀመሩትን ጥረት ማጠናከር እንዳለባቸው አመልክተዋል።
የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት መሳተፍ ይጠበቅባቸዋል
Feb 28, 2026 89
ሰመራ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት መሳተፍ እንደሚጠበቅባቸው የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ገለፀ። ፌዴሬሽኑ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ታዛቢዎችን ለማሰማራት በአፋር ክልል ክላስተር ደረጃ የታዛቢዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናውን ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር ገነት ስዩም እንደተናገሩት ሴቶች በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ ሁኖ እንዲጠናቀቅ ሀላፊነታቸው መወጣት አለባቸው። ሴቷ ለመመረጥም ይሁን ለመምረጥ እንዲሁም በታዛቢነት ተሳትፎዋን ማሳደግ እንድትችል የአሰልጣኞች ስልጠናው ጉልህ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል። ላለፉት ዓመታት ምርጫዎችን በመታዘብና ግንዛቤ በመስጠት የተሳተፈው ፌዴሬሽኑ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት በማሳደግ ረገድም ሰፋፊ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ገልፀዋል። የመራጮችን ግንዛቤ ከማሳደግ አንጻር በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በተለያዩ አማራጮች በመጠቀም የማህበረሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ተናግረዋል። የአፋር ክልል ሴቶች ፌዴሬሽን ዳይሬክተር ፋጡማ ሐንፈሬ በበኩላቸው እየተሰጠ ያለው የአሰልጣኞች ስልጠና ቀጣዩ ምርጫ ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚያግዝ ነው።
ምርጫው ለዴሞክራሲ ስርዓት መጎልበትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ጥሩ መሰረት እንዲያኖር የፖለቲካ ፓርቲዎች መስራት ይገባቸዋል
Feb 28, 2026 76
መቱ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጎልበትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ጥሩ መሰረት እንዲያኖር የፖለቲካ ፓርቲዎች መስራት እንደሚገባቸው ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የምርጫ ሂደቱም ነፃ፣ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፓርቲዎች የምርጫ ህጉን አክብረው እንዲሰሩ አስገንዝቧል። አጠቃላይ የምርጫ ሂደቱንና የፓርቲዎችን ሃላፊነት በተመለከተ ኢዜአ በመቱ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራንን አነጋግሯል። በዩኒቨርሲቲው የሕግ ትምህርት ቤት ዲን ዩሱፍ ጋዛሊ፤ የምርጫ ዴሞክራሲያዊነት መለኪያው ሂደቱና የፓርቲዎች ሰላማዊና ደሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በቅድመ ምርጫ ፓርቲዎች የምርጫ ስነ ምግባር ደንቡን በማክበር የመወዳደሪያ ሐሳባቸውን ለሕዝብ በመሸጥ ተቀባይነት ለማግኘት መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። ፓርቲዎች የሃሳብና የፖሊሲ ክርክር ላይ ማተኮር እንዳለባቸውም ተናግረዋል። በምርጫው መሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብትና የዜግነት ኃላፊነት በመሆኑ በሂደቱ ለሀገር ሕልውናና ቀጣይነት ቅድሚያ ሰጥተው መስራት ግደታ እንዳለባቸውም አንስተዋል። በመሆኑም የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጎልበትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ጥሩ መሰረት አኑሮ እንዲያልፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች መስራት ይገባቸዋል ነው ያሉት። በዩኒቨርሲቲው የሥነ-ባሕርይ እና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ መምህር ወንዱ መብራቴ፤ በምርጫው የሚፎካከሩና የሚሳተፉ ሁሉ ከምንም በላይ የሀገርን ሰላምና ህልውና ጉዳይ ቅድሚያ መስጠት ግደታ አለባቸው ብለዋል። በምርጫው ሂደት ፓርቲዎች በሀሳብ የበላይነት ለመወዳደር ዝግጁ ሆነው አሸናፊ ሃሳብ ይዘው ሊመጡ እንደሚገባም ገልጸዋል። በመሆኑም ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲካሄድ የሚፎካከሩ ፓርቲዎችና ደጋፊዎች የየበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ድምጽ አሸናፊ የሚሆንበት ለማድረግ በትኩረት እየሰራን ነው - ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች
Feb 28, 2026 136
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ድምጽ አሸናፊ የሚሆንበትና የሕዝብ ፍላጎት የሚንጸባረቅበት እንዲሆን በትኩረት እየሰሩ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገው የጊዜ ሰሌዳ ያሳያል። ቦርዱ ምርጫውን ማካሄድ የሚያስችሉ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ሲሆን የመራጮች ምዝገባም ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ያካሂዳል። ፓርቲዎችም ዕጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን ምርጫ አስፈጻሚዎች የአሰልጣኞች ሥልጠናም በቦርዱ በኩል እየተሰጠ ይገኛል። በቅርቡ ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕጩዎች የሥነ ምግባር ደንብም አዘጋጅቷል። ምርጫውን ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ተዓማኒ ለማድረግ ያለመውን የሥነ ምግባር ደንብ ፓርቲዎች ፈርመውታል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምርጫው የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጥበት እንዲሆን እየሰሩ ነው። የአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሊቀ መንበር ተስፋሁን ዓለምነህ፤ ፓርቲው በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በርካታ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ምርጫው የሕዝብ ፍላጎት የሚንጸባረቅበት፤ ሕዝብ አሸናፊ የሚሆንበት አካሄድ ተከትለን በምርጫው ለመሳተፍ ዝግጁ ነን ብለዋል። ምርጫው በሂደቱም፣ በውጤቱም ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ተዓማኒ መሆን ይኖርበታል ያሉት አቶ ተስፋሁን በዚህ ረገድ ፓርቲያቸው የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው በምርጫው መወዳደር የሚያስችለውንና አማራጭ ሀሳብ የያዘውን ፕሮግራም መቅረጹን ጠቅሰው በምርጫው ለዲሞክራሲ ሥርዓት መጎልበት የበኩሉን አሻራ ለማሳረፍ ተግቶ ይሰራል ብለዋል። የሲዳማ አንድነት ፓርቲ ሊቀ-መንበር ለማ ኦያቶ በበኩላቸው፤ ፓርቲው ዕጩዎቹን ማስመዝገቡንና ለፓርቲው አባላት የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠቱን አስታውቀዋል። ምርጫው ሠላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ ፓርቲው የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አስረድተዋል። የወለኔ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር ፈይሰል አብዲላዚዝ እንደገለጹት፤ ለምርጫው ስኬታማነት የቦርዱን እንዲሁም የሀገሪቱን ሕግ አክብሮ መንቀሳቀስ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ፓርቲው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በቅርቡ ይፋ ያደረገውን የዕጩዎች የሥነ ምግባር ደንብ መፈረሙን ጨምረው ጠቁመዋል። ተፎካካሪ ፓርቲዎች መሰል የሥነ ምግባር መርሆዎችን በመከተልና በመተግበር ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክራቸውን የሀገርን ልማትና የህዝብን አብሮነት ማዕከል ባደረገ መልኩ ማካሄድ አለባቸው
Feb 27, 2026 150
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የርዕዮተዓለም የምርጫ ክርክራቸውን የሀገርን ልማትና ዕድገት፣ የህዝብን አብሮነት እና መስተጋብር ማዕከል ባደረገ መልኩ ማካሄድ እንደሚኖርባቸው አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በምርጫው የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን አማራጮች የመወዳደሪያ ምልክትና ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም በምርጫው ድምጽ መስጠት የሚችሉበትን ካርድ ለመውሰድና ይበጀኛል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እየተጠባበቁ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችም፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለህዝብ የሚያቀርቧቸው የምርጫ ቅስቀሳና ክርክሮች ከስሜት ይልቅ ዕውቀትና ምክንያታዊነትን ያስቀደሙ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኅን በኩል በክርክሮች ላይ የሚያቀርቧቸው አማራጭ የፖሊሲ ሀሳቦችና በቀጣይም የምረጡኝ ቅስቀሳዎች ዜጎች ይበጀኛል ለሚሉት ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል። አቶ ከድር ሰኢድ እንደገለጹት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ የክርክር መድረኮቹ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማትና ዕድገት አዋጭ የሆኑ ሃሳቦችን ያነገቡ የፖለቲካ ድርጅቶችን ለይቶ ድምጽ ለመስጠት ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። በዘንድሮው ምርጫ ላይ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ክርክር ወቅትም ህዝብን የሚመጥን በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ሃሳቦችን ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ውበት ደጉ በበኩሏ፤ ምርጫ ዜጎች ይበጀኛል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ የሚሰጡበት የአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት መገለጫ ነው ብላለች። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክርም የሀገርን ልማትና ዕድገት፣ የህዝብን አብሮነትና ዘላቂ ሰላም ግንባታ ማዕከል ማድረግ እንደሚኖርበት ገልጸዋል። ህዝቡም በመገናኛ ብዙሃን የሚተላለፉ የምርጫ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎችን ክርክርን በመከታተል ሀሳባቸውን ከብሄራዊ ጥቅም አኳያ መፈተሽ እንዳለበት አመልክተው፤ ለሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊነት ገንቢ ሚና መወጣት እንዳለበት ተናግረዋል። አቶ አማን ማሞ በበኩላቸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ የህዝብን አንድነትና ሰላም ባከበረና በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ መሆን አለበት ብለዋል። ምርጫ የጠንካራ መንግስት ምስረታ፣ የሰላማዊ ፉክክርና የዴሞክራሲ ሥርዓት መገለጫ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ትዕግስት ማሞ ናቸው። በዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ክርክር ወቅት ዕውቀትና የሀገርን ቀጣይነት የሚያስቀድሙ ሃሳቦችን ለህዝቡ በመሸጥ ለምርጫው ዴሞክራሲያዊነት በኃላፊነት መንፈስ መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ገልጸዋል። መራጩ ህዝብም ለሀገርና ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይሰራል ይበጃል ለሚለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት የሚችሉት የምርጫ ክርክሩንና የቅስቀሳ መርሃ ግብሩን ሲከታተሉ መሆኑን ነው የተናገሩት።
በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Feb 27, 2026 104
ሆሳዕና፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች መመዝገባቸውን የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ባደረጋቸው ጥረቶች የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ያስቀጥላል በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲ ምህዳርን በማጠናከር አዲሷን ኢትዮጵያን ለመገንባት ሚናው የጎላ መሆኑም ተመላክቷል። ብልጽግና ፓርቲ የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን (የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ለህዝብና ለአባላቱ አስተዋውቋል፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ በዚህ ወቅት እንዳሉት ብልጽግና ፓርቲ በድህነት ቅነሳ ላይ ባከናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል። ፓርቲው የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሀሳቦችን በማቅረብና ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ጭምር በትብብር በመስራት ስኬት እያስመዘገበ መሆኑንም አስታውሰዋል፡፡ በዞኑ በሰላም ግንባታ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በጤናና በትምህርት ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ ወጤት እየተመዘገበ ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከድህነት በመውጣት በምግብ ራስን ለመቻል በተተገበሩ የሌማት ትሩፋት መርሀግብርና ሌሎች ኢኒሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት መምጣቱንም ጠቁመዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በፓርቲው መሪነት በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ የልማት ሥራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ነው ያስታወቁት። በዞኑ በልማትና በመልካም አስተዳደር በተሰሩ ሥራዎች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የፓርቲው አመራሮችና አባላት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የሀዲያ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ግዛው በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግሥት የፖለቲካ ስልጣን ቅቡልነት በህዝብ ድምፅ ብቻ እንዲወሰን ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በሀገሪቱ የተጀመረውን የዴሞክራሲ ምህዳር በማጠናከር ለአዲሷ ኢትዮጵያ ግንባታ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የፓርቲው አባላት ተሳትፈዋል፡፡
ምርጫው ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው- ፓርቲዎች
Feb 27, 2026 106
ደሴ ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድና ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክሮች ለሀገርና ህዝብ በሚጠቅሙ የፖሊሲ አጀንዳዎች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል በአማራ ክልል ደሴ ከተማና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በደሴ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂደዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢና በኢዜማ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ሻምበል ደምሌ ተረፈ፤ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት መዳበርና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ምርጫ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ የጋራ ምክር ቤቱ የዘንድሮው ምርጫ በሃሳብ የበላይነት በመፎካከር ሀገርን አሸናፊ የሚያደርግ እንዲሆን ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድና ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው ሲሉም ተናግረዋል። የዛሬው ውይይት ዋነኛ ዓላማም በምርጫው ሂደት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በጋራ በመፍታት ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ማካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢና በብልጽግና ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁ፤ ለምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የጋራ ምክር ቤቱ አባላት በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። ለምርጫው ተወዳዳሪ እጩዎችንና ታዛቢዎችን መመልመላቸውን ጠቁመው በቅስቀሳ ወቅት ከጠብ አጫሪነትና ጥላቻ ንግግሮች በመራቅ መራጩ የጠራ ግንዛቤ አግኝቶ እንዲወስን ማድረግ የሁላችንም ሃላፊነት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባልና የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ተወካይ አቶ ያለው አሸብር፤ በሀገር ዘላቂ ሰላም፣ ጥቅምና ልማት ፓርቲያችን አይደራደርም ብለዋል። በወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ መሀመድ የሱፍ፤ በቅደመ ምርጫ፣ በምርጫና በድህረ ምርጫ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማስተካከል የዛሬው ምክክር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በሁሉም ፓርቲዎች ዘንድ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማስተካከል የተሳካ ምርጫ ለማካሄድ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።
ማህበራዊ
ፈተናዋን የተሻገረች ተስፈኛ ሴት ማፍሪያ ማዕከል የሆነው - ለነገዋ
Feb 28, 2026 51
ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል በተለያየ የሙያ መስክ ያሰለጠናቸውን የአራተኛ ዙር ሰልጣኞች አስመርቋል። በመርሃግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ሌሎች የከተማ አስተዳደሩ አመራር አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ወጣት ቤተልሄም በቀለ የአባቷ ህይወት ማለፍ እንዲሁም የእናቷ አቅም ማጣት ከኑሮ ጫና ጋር ተደማምሮ ትምህርቷን ጨርሳ ወደ ስራ እንድትሰማራ አላስቻላትም። ግራ በገባት ጊዜ መንገዷን ሊያቀና ነገዋን ሊያሰምር የሚችለውን መስመር ስትሻ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከልን አገኘች። በማዕከሉ በፋሽን ዲዛይን በመሰልጠንም በዛሬው እለት የእጅ ስራዋ በሆነው ጥበብ ደምቃ ለምረቃ በቅታለች። በቀሰመችው እውቀትና ክህሎት ተግታ ነገ ላይ የተሻለ ሆኖ መገኘትን እንደምትፈልግና ለዚህም ውጥን መሰነቋን ገልጻ፤ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ያሉ ሴቶች ነገ የተሻለ አለና በርቱ ተስፋን ሰንቃችሁ ተጓዙ የሚል ምክርን ለግሳለች። በዛሬው እለት ስልጠናቸውን ካጠናቀቁ ሴቶች መካከል አስቴር አለማየሁ በበኩሏ በማዕከሉ የሙያ ባለቤት ሆኛለሁ ብላለች፡፡ በሰለጠነችበት ዘርፍ ውጤታማ ለመሆን እንደምትፈልግ በመግለጽ፤ ለዚህም ተስፋ ባለመቁረጥ በቀጣይ ጠንክራ እንደምትሰራ ተናግራለች። ከዚህ ቀደም በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋ ለዚህ መድረሷን የምትገልፀው ደግሞ ሌላዋ በማዕከሉ ሰልጥና የሙያ ባለቤት የሆነችው ነፃነት እጅጉ ነች፡፡ በማዕከሉ እውቀትና ክህሎት ከመገብየቷ ባለፈ ስራ በማግኘቷ ደስተኛ መሆኗንና በቀጣይም በርትታ በመስራት ለሌሎች መትረፍን የረዳትን ማህበረሰብን ማገልገል እንደምትሻም ተናግራለች። የለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ከተማ አስተዳደሩ የሚሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች ማሳያ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ሂርጳሳ ጫላ(ዶ/ር) ናቸው። ማዕከሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ስነ ልቦናዊ ድጋፍ የሚሹ ሴቶችን በማሰልጠን ወደ ስራ እንዲገቡ ማስቻሉን ጠቁመው፤ በአራተኛው ዙር ስልጠና የወሰዱ 909 ሴቶች ለምረቃ መብቃታቸውን ተናግረዋል። ሰልጣኞች የንድፈ ሃሳብና የክህሎት ስልጠና አጠናቀው የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ወስደው 97 ነጥብ 5 በመቶ በላይ ማለፋቸውንም ገልጸዋል። እስካሁኑ ባለው የስልጠና ሂደትም 2ሺህ 401 ሴቶችን ማሰልጠኑንና ሰልጣኞች የተሃድሶና የሙያ ስልጠና ማግኘታቸውን ገልፀዋል። ማዕከሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ስነልቦናዊ ድጋፍ ለሚሹ ሴቶች የሚሰጠውን ስልጠና ለማስፋት ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ የአደባባይ ኢፍጣር መርሃ-ግብር ይካሄዳል
Feb 28, 2026 68
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ የ1447ኛው የረመዳን ፆም ወርን ምክንያት በማድረግ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ የሚካሄድ ታላቅ የአደባባይ ኢፍጣር መርሃ-ግብር ማዘጋጀቱን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታወቀ። ምክር ቤቱ መርሃ-ግብሩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ እንዳመለከተው፣ የዘንድሮው የኢፍጣር መርሃግብር "ነጃሺ ለሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እና በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በተመሳሳይ ቀን የሚከናወን ይሆናል። የጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ በመግለጫው ወቅት እንደተናገሩት፤ ረመዳን የአብሮነት፣ የከፍታ እና የጋራ እሴቶቻችን የሚጠናከሩበት ወር ነው። በመሆኑም የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ የአደባባይ ኢፍጣር መርሃ-ግብር እንደሚካሄድ ገልጸው፤ መርሃ-ግብሩ የመተሳሰብ እና የመረዳዳት እሴቶችን የሚያጎለብት ነው ብለዋል። በተጨማሪም መርሃ-ግብሩ ለሀገሪቱ የከፍታ ጉዞ የሚጠበቅብንን አስተዋጽኦ ለማበርከት ቃላችንን የምናድስበት ነው ብለዋል። ይህንን መርሃ-ግብር በበላይነት የሚያስተባብረው በጠቅላይ ምክር ቤቱ ስር የሚገኘው የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል መሆኑን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዝዳንት ኡስታዝ ሀይደር ከድር በበኩላቸው፣ የዘንድሮው ኢፍጣር በዓይነቱ ለየት ያለና በአንድ ቀን በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚካሄድ መሆኑን ገልጸው፤ ወጣቶች ለአንድነት፣ ለልማትና ለእድገት ያላቸውን ሚና የሚያጠናክሩበት መድረክ እንደሚሆንም አክለዋል። የጠቅላይ ምክር ቤቱ የዑለማ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሼህ ዓሊ መሐመድ ኤባ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በእለቱ አቅም የሌላቸውን ወገኖች ማገዝ እና መደገፍ በፈጣሪ ዘንድ እጅግ የሚወደድ ተግባር በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። መርሃ-ግብሩ በዋናነት ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓቶችን ከመፈጸም ባለፈ፣ ለሀገራዊ አንድነትና ለዘላቂ ሰላም በጋራ ፀሎት የሚደረግበት ታላቅ መድረክ እንደሚሆን ገልፀዋል።
ማዕከሉ የጥቁር ህዝቦችን ክብር፣ ባህልና ቅርስ ለማስጠበቅ የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
Feb 28, 2026 80
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፉ የጥቁር ህዝቦች ማዕከል የጥቁር ህዝቦችን ክብር፣ ባህልና ቅርስ ለማስጠበቅ የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። ዓለም አቀፉ የጥቁር ህዝቦች ማዕከል ዓመታዊ የምክር ቤት ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል። በጉባዔው ላይ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴን ጨምሮ ለጥቁር ህዝቦች ትግል ፋና ወጊ ሚና ስትጫወት ቆይታለች። የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ትግል እርሾ የሆነው የዓድዋ ድል ለዚህ ተጠቃሽ ነው ብለዋል። ዓለም አቀፉ የጥቁር ህዝቦች ማዕከል መቀመጫው ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑ ለጥቁር ህዝቦች መብት ትግል ያላትን ቁርጠኝነት ያመላከተ መሆኑን ተናግረዋል። ማዕከሉ የጥቁር ህዝቦች ክብር፣ ቅርሶችንና ባህል ለማስጠበቅ የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። ማዕከሉ አፍሪካውያንና በመላው ዓለም የሚገኙ የጥቁር ዝርያ ያላቸው ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ስራዎቻቸውና አሻራዎቻቸው ታትመውና ተሰንደው የሚቀመጡበት የጥናትና ምርምር እንዲሁም የህትመት ማዕከል ሊኖረው እንደሚገባም ጠቁመዋል። አሁን ላለው እና ለመጪው ትውልድ እሴቶችና የተለያዩ እውቀቶችን ማሸጋገር ላይ ማዕከሉ ተግቶ ሊሰራ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መንግሥትም ማዕከሉ የተቋቋመለትን ዓላማ እንዲያሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የዓለም አቀፉ የጥቁር ህዝቦች ማዕከል ጀነራል ካውንስል ፕሬዝዳንትና የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፤ የማዕከሉን ዓላማ ለማሳካት ከተቋማትና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ብለዋል። የጥቁር ህዝቦች ታሪክ በማጉላት የተደበቁና በዓለም ደረጃ ጎልተው ሊነገሩ የሚገባቸው ትርክቶችን ጥናት ላይ ተመስርቶ ማውጣት ዙሪያ እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። ተተኪው ትውልድ በቅድመ አያቶች ታሪክ መነሻነት የራሱን ታሪክ የሚጽፍበትን ዕድልና ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ለዜጎች ክብር መጠበቅ፣ ለቅርስና ትውልዱ ዕሴት ማሸጋገር ላይ የጀመራቸው ስራዎች እንዲሳኩ ሚኒስቴሩ ተባብሮ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። ለዚህም ሚኒስቴሩ ከማዕከሉ ጋር በጋራ ለመሥራት ሥምምነት ላይ መድረሱን ጠቁመዋል።
በአባቶቻችን ሉዓላዊነቷ የጸናች ኢትዮጵያን ዳር ድንበር አስከብረን ለማስቀጠል የድርሻችንን እንወጣለን
Feb 28, 2026 81
ደሴ፤ የካቲት 21/2018 (ኢዜአ)፡- በአባቶቻችን ደምና አጥንት ሉዓላዊነቷ የጸናች ኢትዮጵያን ዳር ድንበር አስከብረን ለማስቀጠል የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ የደሴ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ። 130ኛው የዓድዋ ድል በዓልን አስመልክቶ "ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ ተስፋ" በሚል መሪ ሀሳብ በደሴ ከተማ ከወጣቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሂዷል። የምክክሩ ተሳታፊ ወጣቶች ሀገራችን ኢትዮጵያ በአባቶቻችን ደምና አጥንት ሉዓላዊነቷ ጸንቶ መቆየቱን አንስተዋል። ይህን አስከብረን ማቆየት የእኛ ድርሻ በመሆኑ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። ከወጣቶቹ መካከል ወጣት ሰይድ አህመድ እንደገለጸው፣ ዓድዋ የመላው ጥቁር ህዝቦች የነጻነት አርማ፣ የአሸናፊነት ምልክትና የአንድነት ውጤት ነው። አባቶቻችን በውጭ ወራሪ ጠላት ላለመገዛትና ሀገራቸውን ላለማስደፈር አጥንታቸውን ከስክሰው እና ደማቸውን አፍስሰው ያስረከቡንን ሀገር ዳር ድንበር ለማስጠበቅ የድርሻችንን እንወጣለን ብሏል። ትክክለኛ ታሪኩን በውል ተረድተን አንድነታችንንና ሰላማችንን በመጠበቅ ለሀገራችንም ሆነ ለከተማችን ብልጽግና የራሳችንን አሻራና ታሪክ እንሰራለን ብሏል። ሌላዋ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣት ማህሌት ይመር በበኩሏ፣ ቅድመ አባቶቻችንና እናቶቻችን የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ለማስከበር የከፈሉት መስዋዕትነት ለዛሬ ነጻነት አብቅቶናል ብላለች። እኛም ከዓድዋ ድል አንድነትን፣ ጀግንነትንና ህበረ ብሄራዊነትን ተምረን በሰላምና በልማት የራሳችንን ድል ለማስመዝገብ እየሰራን እንገኛለን ብላለች። አንድነቷ፣ ነፃነቷና ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ የተረከብናትን ሀገር እኛም ለቀጣዩ ትውልድ እናስተላልፋለን ብላለች። ከዓድዋ ድል አንድነትን፣ አሸናፊነትን፣ ቅንጅትንና ብርታትን ተምረን እኛም በዘመናችን የውስጥና የውጭ ጠላቶቻችንን በጋራ ድል አድርገን ታሪክ እንሰራለን ያለችው ደግሞ ወጣት ሸዊት ቴዎድሮስ ናት። ከመንግስት ጎን ተሰልፈንም የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶችና የወደባችን ጥያቄ መልስ እንዲያገኝ የሚከፈለውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈል ዝግጁ ነን፣ ለዚህም የዓድዋ ድል አስተምሮናል ብላለች። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፣ ወጣቱ ትውልድ አንድነቱንና ሰላሙን ጠብቆ በዘመኑ የራሱን ድልና ታሪክ ሊያስመዘግብ ይገባል ብለዋል። ከዓድዋ ድልም አንድነትና መደማመጥን ተምሮ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በጋራ መጠበቅና የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችና ልማቶችን በመደገፍ የብልጽግና ጉዞ ዳር እንዲደርስ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል። ዓድዋ የመላው ጥቁር ህዝቦች ድል፣ ነጻነት፣ አሸናፊነትና አንድነት መሆኑን አስታውሰው፣ ዘወትር ሲዘከር የሚኖር የኢትዮጵያዊያን የአንድነት ምስጢርና ውጤት መሆኑንም ተናግረዋል። በመድረኩ የደሴ ከተማ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢኮኖሚ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 27 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ሥራ ገብተዋል
Feb 28, 2026 80
ጎንደር፤ የካቲት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 27 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ሥራ እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን የዞኑ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ። አሀዱ ቢዝነስ ግሩፕ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ በ112 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያቋቋመው የቅባት እህሎች ማበጠሪያና ማቀናበሪያ ፋብሪካ ተመርቋል። በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ የመምሪያው ሃላፊ አቶ የአብስራ እሸቴ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በዞኑ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ችግር በመፍታት በሙሉ አቅማቸው ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩ እየተደረገ ነው። ንቅናቄውን ተከትሎ 27 ኢንዱስትሪዎች ወደማምረት ሥራ መግባታቸውን ገልጸው ባለፉት ስባት ወራት ብቻ በምግብ ዘይት፣ በጨርቃ ጨርቅና በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ሰባት አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል። አምራች ኢንዱስትሪዎቹ የማምረቻ ማሽኖችን ከውጪ ከቀረጥ ነጻ እንዲያስገቡ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር ጀምሮ ከ189 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ከፋይናንስ ተቋማት ብድር እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመዋል። ወደ ምርት ሥራ የገቡት አምራች ኢንዱስሪዎችም ከ300 በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የሥራ እድል መፍጠራቸውንም ነው አቶ የአብስራ የገለጹት። በዓመቱ እስካሁን ድረስ 7 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ካፒታል ላስመዘገቡ 76 ባለሀብቶችም የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል። ፈቃድ የተሰጣቸው ኢንቨስትመንቶች ወደማመረት ሲሸጋገሩ ከ10 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩም ገልጸዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ በበኩላቸው እንዳሉት በዞኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ በመደረጉ ለበርካታ ወገኖች የሥራ እድል እየተፈጠረ ነወ። ዞኑ በአግሮ ኢንዱስትሪ ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች በጥሬ እቃነት ሊውሉ የሚችሉ የቅባትና የጥራጥሬ ሰብሎች በስፋት የሚመረትበት አካባቢ መሆኑንም አስረድተዋል። የአሀዱ ቢዝነስ ግሩፕ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ብርሀኑ ባዩህ ፋብሪካው በ112 ሚሊዮን ብር ካፒታል መቋቋሙን ገልጸዋል። በቀን 800 ኩንታል ሰሊጥና አኩሪ አተር አቀናብሮና አሽጎ ለዓለም ገበያ የማቅረብ አቅም እንዳለውም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በፋብሪካው ለ20 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው፣ በቀጣይም የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ በመክፈት ከውጪ የሚገባን ዘይት ለመተካት መታቀዱን ተናግረዋል። ፋብሪካው በዓመት ከ290 ሺህ ኩንታል በላይ ሰሊጥና አኩሪ አተር በግብአትነት እንደሚጠቀም ገልጸው፣ ይህም ለአምራች አርሶ አደሮች ሰፊው የገበያ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል ። በፋብሪካው የምረቃ ሥነስርዓት ላይ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው ባለሀብቶች ተገኝተዋል።
በአማራ ክልል ህገ-ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከል የሚደረገው የተቀናጀ ጥረት ውጤት እያስገኘ ነው
Feb 28, 2026 54
ባህርዳር፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ህገ-ወጥ ንግድንና ኮንትሮባንድን በተቀናጀ አግባብ በመከላከል የህግ ተገዥነትን ለማረጋገጥ እየተከናወነ ያለው ስራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ የምርትና ግብይት፣ የገበያ አረጋጊ፣ የፀረ-ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ጥምር ግብረ-ኃይል፤ የወንጀል ጉዳዮች ቴክኒክ ኮሚቴ የሥራ አፈጻጸም ግምገማውን ዛሬ በባህርዳር ከተማ አካሂዷል። በቢሮው የኢኮኖሚ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክተር ሙሉጌታ አሻግሬ እንደገለጹት፤ የቴክኒክ ኮሚቴው 13 ተቋማትን በማቀፍ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል በቅንጅት እየሰራ ይገኛል። በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት በህገ-ወጥ ተግባር ተሰማርተው በተገኙ 190ሺህ 150 የንግድ ድርጅቶችና ማህበራት ላይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ፣ የሥራ እገዳና የንግድ ፈቃድ ስረዛ እርምጃዎች ተወስደዋል ብለዋል። ምርቶችን በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ውስጥ ሲያስገቡና ወደ ውጭ ሲያስወጡ ተይዘው በተገኙ 128 ነጋዴዎች ላይ ደግሞ እስከ 12 ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት ተላልፏል ነው ያሉት። ይህ ውጤት ሊመዘገብ የቻለው በተቋማቱ መካከል ያለውን የመረጃ ልውውጥና የጋራ ቁጥጥር በማጠናከር መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢብራሂም መሀመድ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጤናማ ለማድረግ ህገ-ወጥ የኬላ ቀረጥ፣ የኮንትሮባንድ ዝውውርና የነዳጅ ስርጭት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፈው ሳምንት ብቻ 34 ሰዎች ነዳጅን ከማደያ አውጥተው በህገ-ወጥ መንገድ ሲያጓጉዙ እጅ ከፈንጅ መያዛቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደጀን ወዳጅ፤ የነዳጅ፣ የጦር መሳሪያ፣ የመድኃኒትና የምግብ ነክ ምርቶች ህገ-ወጥ ዝውውርን ለማስቆም የተከናወነው ስራ አበረታች መሆኑንና በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በክልሉ በግብርና ልማት ሥራዎች የታየው እድገትና ማንሰራራት ቀጣይነት እንዲኖረው የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Feb 28, 2026 115
አዳማ ፤የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በግብርና ልማት ሥራዎች የታየው እድገትና ማንሰራራት ቀጣይነት እንዲኖረው የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ከሁለት ሺህ በላይ በየደረጃው የሚገኙ የግብርና ዘርፍ አመራሮች እና ባለሙያዎች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በአዳማ ገልመ አባገዳ ተካሄዷል። የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ እንደገለፁት በበጋ መስኖ ስንዴ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ሌሎች የግብርና ልማት ሥራዎች የታየው እድገትና ማንሰራራት ቀጣይነት እንዲኖረው ጥረት እየተደረገ ነው። ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሥራዎች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሻገርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዙ መሆናቸውንም ገልጸዋል። በተለይም በኢኒሼቲቭ እየተተገበሩ የሚገኙ የግብርና ልማት ስራዎች በስኬታማነት እንዲቀጥሉ የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል። በክልሉ በበጋ መስኖ ስንዴ፣ በሩዝ፣ በቡናና በሻይ ቅጠል ልማት፣ በአቮካዶ፣ ሙዝ፣ ወተትና ዓሣ ሀብትን ጨምሮ በእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ተጨባጭ ውጤት መምጣቱን ተናግረዋል። በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ከ3 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት መሸፈኑን ጠቅሰው ዕቅዱ እንዲሳካ በማድረግ ረገድ በየደረጃው ያሉ ሙያተኞችና አመራሮች ሚናቸው የጎላ እንደሆነ ገልጸዋል። በክልሉ መጪው የበልግ እና የ2018/19 የመኸር አዝመራን ለማሳካት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ከወዲሁ እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። ያለን ዕውቀት፣ ክህሎትና ልምድ በማቀናጀት የተሻለ ምርት ለማግኘት ጠንካራ ሥራ እንደሚሰራ ገልጸው በዘንድሮ የበልግ አዝመራ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት 46 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን አንስተዋል። ለ2018/19 የምርት ዘመን በመኸር እርሻ 11 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዋና ዋና ሰብሎች ለመሸፈንና 372 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ጠቅሰዋል። እንደ አቶ ጌቱ ገለጻ በክልሉ በበልግና በመኸር ከሚለማው መሬት ውስጥ 9 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው መሬት በኩታ ገጠም የሚለማ ነው። የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በመጪው በልግና በመኸር እርሻ በተለይ ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች ላይ ማተኮር ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም የግብርናው ዘርፍ የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትን እንዲቋቋም እርሻን ከተፈጥሮ ዝናብ ጥገኝነት ማላቀቅ የሚያስችል ስራን ማስፋት እንደሚገባም አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሣ (ፕሮፌሰር) እንደገለፁት የምርምርና የቴክኖሎጂ ውጤቶቻችን የአርሶ አደሩ ህይወት መለወጥ የሚችሉ መሆን እንዳለባቸው ገልጸዋል። የምርምር ውጤቶች አርሶ አደሩ ዘንድ ደርሰው ህይወቱ እንዲለወጥ ለማስቻል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ ገልጸው ለዚህም ኢንስቲትዩቱ በምርምር የሚያወጣቸውን ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ ያደርጋል ብለዋል።
ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም መከበር ለልማትና ከድህነት የመውጣት ጥረት ስኬት በተደመረ አቅም መስራት ይገባል
Feb 28, 2026 73
ሀዋሳ፤ የካቲት 21/2018 (ኢዜአ):-ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም መከበር ለልማትና ከድህነት የመውጣት ጥረት ስኬት በተደመረ አቅም መስራት እንደሚገባ ምሁራን ገለጹ። ብሔራዊ ጥቅም በአንድ አገር ውስጥ የሚኖር ሕዝብና መንግሥት የሀገሪቱን ደኅንነት፣ ሉዓላዊነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና ማኅበራዊ ደኅንነት ለማስጠበቅ የሚሠሩባቸው መሠረታዊ ግቦች መሆናቸው ይታወቃል። በተለይም የሀገርን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት ከማንኛውም ጥቃት መከላከል፤ የሕዝብን የኑሮ ደረጃ የሚያሻሽሉ የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የሀብት ልማት ሥራዎችን ማስፋፋት የግድ ይላል። የዜጎችን ክብር፣ ሰላምና ደኅንነት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የማረጋገጥ ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅምና የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ መርህ ተደርጎ እየተሰራበት መሆኑም ይታወቃል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ኢትዮጵያ የምትገኝበት የምስራቅ አፍሪካ ቀንድና የቀይ ባህር ቀጣና የብዙ ኃይሎች ፍላጎት ያለበት መሆኑን ይገልፃሉ። በመሆኑም ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም መከበር ለልማትና ከድህነት የመውጣት ጥረት ስኬት በተደመረ አቅም መስራት እንደሚገባ ያስረዳሉ። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ታፈሰ ማቴዎስ (ዶ/ር)፤ ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው ዓለም ዓቀፋዊ ሁኔታ ውስጥ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር የህልውና ጉዳይ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያነሳችው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት ያለው መሆኑን የጠቀሱት ምሁሩ ጥያቄው ምላሽ ማግኘት እንዲችል በጋራ መቆም ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል። ባለፉት ዘመናትም ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር እንድትርቅ የተደረገው በታሪካዊ ጠላቶች ሴራ ብቻ ሳይሆን ለብሔራዊ ጥቅም መከበር በጋራ አለመቆማችን በመሆኑ በቀጣይ የባህር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ሌሎች ብሔራዊ ጥቅሞችን ለማስከብር መተባበር አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል። ሌላው በዩኒቨርሲቲው የጂኦግራፊና አካባቢ ጥናት መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ምስራቅ ታምሬ (ዶ/ር) የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር የፖለቲካ ልዩነት ሳይገድበን በአንድነት መቆም ይገባል ሲሉ ገልጸዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲጠናቀቅ መላው ኢትዮጵያዊ ያሳየውን ቁርጠኝነት የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄን ለመመለስም መድገም አለበት ብለዋል። በተመሳሳይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር)፤ ብሔራዊ ጥቅም ከሀገር ህልውና ጋር የተያያዘ በመሆኑ ሁሉም በጋራ መቆም እንዳለበት መክረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት ይገባል
Feb 28, 2026 73
ዲመካ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፡- በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አገኘሁ ተሻገር፤ በደቡብ ኦሞ ዞን ዲመካ ከተማ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለሚገነባው የአርብቶ እና ከፊል አርብቶ አደር የምርምር ኢንስቲትዩት የመሰረተ ድንጋይ አኑረዋል። ዩኒቨርሲቲው የማዕከሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ የምርምር ስራውን መጀመር ይጠበቅበታል ያሉት አፈ ጉባኤው ሀገር በቀል ዕውቀቶችን በመጠቀም በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሀብቶችን በሳይንሳዊ ምርምር በማስደገፍ የላቀ ጥቅም እንዲሰጡ ማድረግ ይገባል ብለዋል። የምርምር ማዕከሉ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች ብቻ የሚጠቀሙበት ሳይሆን በሀገር ውስጥ እና በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚገኙ ተመራማሪዎች የሚሳተፉበትና ልምድ የሚለዋወጡበት እንደሚሆን ገልጸዋል። የምርምር ማዕከሉ በተያዘለት ጊዜ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለሚፈለገው ዓላማ እንዲውል አስፈላጊው እገዛ ድጋፍና ክትትል የሚደረግ ይሆናል ብለዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዮሐንስ ይትባረክ (ዶ/ር)፤ የሚገነባው የምርምር ማእከል በዋነኝነት አራት መሰረታዊ ተልዕኮዎችን ለመፈፀም የሚያስችል ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል። በአካባቢው የግብርና ሥራ እና የእንስሳት ሀብት በሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር በማሳደግ የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ አንዱ ሲሆን የቱሪዝም ሀብትን በምርምር በማገዝ ዓለም አቀፋዊ እውቅና እንዲያገኝ ማድረግም ሌላው መሆኑን አንስተዋል። በአካባቢው ያሉ ሀገር በቀል ዕውቀቶችን የመሰነድ፣ የማስተዋወቅ እና የማሳደግ ተልእኮን ለማሳካትም ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዘርባጃን የሕዝብ አገልግሎት እና ማኅበራዊ ፈጠራ የመንግሥት ኤጀንሲን ጎበኙ
Feb 27, 2026 89
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው የአዘርባጃን የሕዝብ አገልግሎት እና ማኅበራዊ ፈጠራ የመንግሥት ኤጀንሲ (ASAN) የፈጠራ ማዕከልን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ አዘርባጃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የሚመራ አስተዳደርን ለማስፋፋት እና የሕዝብ አገልግሎቶችን በዲጂታል ለማዘመን የምትከተለውን ስትራቴጂያዊ አካሄድ የሚያሳይ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሀገሪቱ የAI ኢንጂነሪንግ እና የአመራር ሥልጠና ዋና ማዕከል የሆነውን የAI አካዳሚን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ልዑኩ ጉብኝቱን በመቀጠል በክልሉ ውስጥ ካሉ ትላልቅ የነዳጅ እና የጋዝ ማቀነባበሪያ ማዕከላት አንዱ ወደሆነው ሳንጋቻል ተርሚናል እና ወደ አላት ነፃ የኢኮኖሚ ቀጣና አምርቷል። ጉብኝቶቹ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢነርጂ እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትብብር ይበልጥ የማጠናከር አቅም እንዳላቸው ጽህፈት ቤቱ ገልጿል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ለማሳለጥ ወጣቶችን በቴክኖሎጂ የማብቃት ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል
Feb 27, 2026 90
አምቦ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ለማሳለጥ ወጣቶችን በቴክኖሎጂ ለማብቃት ስራ ትኩረት መሰጠቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) አስታወቁ። የሰውሰራሽ አስተውሎት ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኦሮሚያ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር በአምቦ ከተማ ያስገነባው የወጣቶች ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ማዕከል እና የአምቦ ስታርት አፕ ማዕከል ተመርቋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ እና ሌሎች የፌዴራል እና የክልል አመራሮች ተገኝተዋል። በዚሁ ጊዜ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፣ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማስቀጠል ወጣቶችን በቴክኖሎጂ፣ በሳይንስና በፈጠራ ለማብቃት ስራ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል። ዛሬ በአምቦ ከተማ አገልግሎት የጀመረው ማዕከልም በአገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የኢኖቬሽን ሥነ-ምህዳር የማጠናከርና የቴክኖሎጂ ክፍተቶችን ለመሙላት ያግዛል ብለዋል። መሰል የኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ማዕከላት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተገንብተው የዜጎችን ችግር እየፈቱ መሆኑን ጠቅሰው የአምቦው ማዕከልም ወጣቶችን በቴክኖሎጂ በማብቃት የማኅበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የፈጠራ ሥራዎች የሚፈልቁበት ይሆናል ነው ያሉት። የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ በበኩላቸው፤ የአንድን ሀገር ዕድገት ማፋጠን የሚቻለው በቴክኖሎጂ ማገዝ ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ መንግሥት ግብርናንና ሌሎች ዘርፎችን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሕዝቡን ኑሮ ለማሻሻልና የሀገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግብ ለማሳካት ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። የአምቦ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃጫሉ ገመቹ፤ ማዕከሉ ወጣቶች የሚዝናኑበት ብቻ ሳይሆን፣ ዕውቀታቸውን ወደ ተግባር በመለወጥ ማኅበረሰባቸውን የሚያገለግሉበት የፈጠራ ማዕከል መሆኑን አብራርተዋል። በማዕከሉ የቴክኖሎጂ ሥልጠና የወሰዱ ወጣቶች በበኩላቸው፣ ባገኙት ዕውቀት ተጠቅመው የሀገሪቱን ዕድገት ለማፋጠን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በተለይም የድረ-ገጽ ማበልጸግ ሥልጠና በመውሰድ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ማኅበረሰብን በፈጠራ ለማገዝ መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።
በከተማዋ በተያዘው በጀት ዓመት ለአንድ መቶ ሺህ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ ለማዳረስ እየተሰራ ነው
Feb 27, 2026 83
ደገሃቡር፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በሶማሌ ክልል ደገሃቡር ከተማ በተያዘው በጀት ዓመት ለአንድ መቶ ሺህ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አብዲሀኪም መአሊን ገለጹ። የደገሃቡር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዲሀኪም መአሊን ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች ወጥ የሆነ ማንነት እንዲኖራቸው በማድረግ የተቀላጠፈና ዘመናዊ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው ፋይዳ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተቀመጠው ሀገራዊ ግብ እንዲሳካና ለዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመት በከተማዋ 100 ሺህ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እስካሁን ከ30 ሺህ በላይ ለሚሆኑት ተደራሽ መደረጉን አመልክተዋል። በከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል። ስልጠናው በቴክኖሎጂ የዳበረ ወጣት ለመፍጠር የላቀ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፣ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ዜጎች የዲጂታል መታወቂያውን በመያዝ ከሚሰጡ ዘመናዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል።
ስፖርት
ሲዳማ ቡና ሃዋሳ ከተማን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ
Feb 28, 2026 42
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐ-ግብር ሲዳማ ቡና ሃዋሳ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብርሃኑ በቀለ እና መስፍን ታፈሰ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ተባረክ ሄፋሞ ለሃዋሳ ከተማ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሲዳማ ቡና በ39 ነጥብ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል። በሊጉ 10ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሃዋሳ ከተማ በ36 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ጨዋታውን ተከትሎ 21ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ22ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከየካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
ቦርንማውዝ እና ሰንደርላንድ ነጥብ ተጋሩ
Feb 28, 2026 50
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ቦርንማውዝ እና ሰንደርላንድ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በቫይታሊቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኤሊዘር ማዬንዳ በ18ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ ሰንደርላንድ መሪ ሆኗል። ከእረፍት መልስ ኢቫኒልሰን በ64ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል ቦርንማውዝን አቻ አድርጋለች። ባለሜዳው ቦርንማውዝ በኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢወስድም ቡድኖቹ ተመጣጣኝ ሊባል በሚችል ሁኔታ ኢላማቸውን የጠበቁ የግብ ሙከራዎችን አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ቦርንማውዝ በ39 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። ቦርንማውዝ ባለፉት ሁለት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። ሰንደርላንድ በ37 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ቡድኑ ባለፉት አራት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም።
ዎልቭስ በሊጉ ሁለተኛ ድሉን አስመዘገበ
Feb 28, 2026 85
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ28ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ዎልቭስ አስቶንቪላን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሞልኒው ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጆአኦ ጎሜዝ በ61ኛው እና ሮድሪጎ ጎሜዝ በ98ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በጨዋታው አስቶንቪላ ብልጫ ቢወስድም ዎልቭስ ያገኛቸውን ግልጽ እድሎች ወደ ግብ በመቀየር ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በሊጉ ሁለተኛ ድሉን ያስመዘገበው ዎልቭስ በ13 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ላለመውረድ የሚያደርገውን ትግል የሚያግዝ ድል አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አስቶንቪላ በ51 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡድኑ ሻምፒዮንስ ለመግባት በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ ጥሏል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት እስከ የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
የሃዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡና የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ
Feb 28, 2026 77
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል። በዕለቱ የሚደረገው ብቸኛ መርሐ-ግብር ሃዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡናን ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ያገናኛል። ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው 20 ጨዋታዎች በ10ሩ አሸንፎ በአራቱ ተሸንፎ በስድስቱ አቻ ወጥቷል። በጨዋታቹ ላይ 23 ግቦችን ሲያስቆጥር 11 ጎሎች ተቆጥረውበታል። የሁለት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ሃዋሳ ከተማ በ36 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና በሊጉ ካካሄዳቸው 20 ጨዋታዎች መካከል በዘጠኙ ድል ሲቀናው ሁለት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ ዘጠኝ ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 24 ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ 10 ጎሎችን አስተናግዷል። ሲዳማ ቡና በ37 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ20ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሃዋሳ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ አንድ አቻ ተለያይቷል። ሲዳማ ቡና ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ያደረገው ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል። ሃዋሳ ከተማ የሊጉ መሪ ለመሆን፣ ሲዳማ ቡና መሪነቱን ለማስጠበቅ የሚያደርጉት ፍልሚያ ተመጣጣኝ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል። ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ የመጀመሪያ ዙር በሁለተኛ ሳምንት ተገናኝተው ሲዳማ ቡና 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው።
አካባቢ ጥበቃ
አዲሱ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ 1383/2017 "ሁሉንም ዓይነት ፕላስቲኮች" ሙሉ በሙሉ አግዷል?
Feb 28, 2026 83
የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የፕላስቲክ ብክለትን በመቀነስ የአካባቢን ደህንነት ለማረጋገጥ ያለመውን አዲሱን የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ 1383/2017 ወደ ትግበራ ማስገባቱ ይታወቃል። ይሁን እንጂ፣ የዚህን አዋጅ መውጣት ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ላይ ማህበረሰቡን የሚያሳስቱ መረጃዎች በስፋት እየተዘዋወሩ ይገኛሉ። በመሆኑም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት እየተሰራጩ ያሉትን ዋና ዋና አሳሳች መረጃዎች በመለየት፤ ከአዋጁ፣ ከኃላፊዎች ማብራሪያ እና ይፋዊ መግለጫዎች ጋር በማገናዘብ መረጃ ማጣራት ተደርጓል። የተሳሳተ መረጃ፡- "ማንኛውም ለአንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውል ፕላስቲክ እንዳይመረት፣ እንዳይገባ እና እንዳይሸጥ ሙሉ በሙሉ ታግዷል" እውነታው፡- አዋጁ ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ፕላስቲኮችን በሙሉ አልከለከለም። በህጉ መሰረት ሙሉ በሙሉ የተከለከሉት ለአንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውሉ "ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶች (ፌስታል)" ብቻ ናቸው። የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 በግልጽ እንደሚያስቀምጠው፤ “ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል ፕላስቲክ እንዲመረት፣ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ ወይም ጥቅም ላይ እንዲውል መመሪያ ሊወስን ይችላል” ይላል። ይህም ማለት እንደየአስፈላጊነቱ የሚፈቀዱ ፕላስቲኮች አሉ። ይህንን ጉዳይ በተመለከተ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ በሰጠው ማብራሪያ፤ የፕላስቲክ ማሸጊያ ማለት እቃዎችን ከብክለት ለመከላከል ወይንም ከሌላ ነገር ጋር እንዳይቀላቀል ለማድረግ የሚጠቅም መሆኑን ጠቅሶ፤ የምግብ፣ የባልትና ውጤቶች፣ የላውንደሪ አገልግሎት እና ሌሎች ምርቶችን ለማሸግ የሚውሉ የፕላስቲክ ማሸጊያዎች በአዋጁ የተፈቀዱ መሆናቸውን አረጋግጧል። የእነዚህ ማሸጊያዎች አወጋገድ በቀጣይ በሚወጡ መመሪያዎች የሚመራ ይሆናል። በተጨማሪም የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሌሊሴ ነሜ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት(ኢዜአ) በሰጡት ማብራሪያ፤ አዋጁ የፕላስቲክ ምርቶችን ሙሉ ለሙሉ የሚከለክል እንዳልሆነ በግልጽ አረጋግጠዋል። የተሳሳተ መረጃ፡- "የቁጥጥር ስራውን የሚያከናውነውና እርምጃ የሚወስደው የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ብቻ ነው" እውነታው፡- አዋጁን የማስፈጸም የበላይ ኃላፊነት የተሰጠው ለአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና ለክልል የአካባቢ ጥበቃ ቢሮዎች መሆኑ እውነት ቢሆንም፤ የቁጥጥር ስራው ግን በባለስልጣኑ ብቻ የሚከወን አይደለም። ህጉ ወደ መሬት ወርዶ ተግባራዊ ሲደረግ፣ በየዕለቱ ህገ-ወጥ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን በሚያመርቱ፣ በሚያስገቡ እና በሚጠቀሙ አካላት ላይ ክትትል የሚያደርጉት እና የቁጥጥር እርምጃ የሚወስዱት የፖሊስ እና የደንብ ማስከበር አካላት መሆናቸውን ዋና ዳይሬክተሯ አብራርተዋል። በመሆኑም ህዝቡ እና የንግዱ ማህበረሰብ የቁጥጥር ስራው በጸጥታና ደንብ አስከባሪ አካላት ጭምር የሚተገበር መሆኑን ሊገነዘቡት ይገባል። ህብረተሰቡ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሱ ያልተረጋገጡ አሳሳች መረጃዎችን ባለመቀበል የፕላስቲክ አጠቃቀምን በተመለከተ የሚወጡ መመሪያዎችን በቀጥታ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ይፋዊ ገጾች እና ከታማኝ ምንጮች ብቻ እንዲወስድ ይመከራል።
የፕላስቲክ ከረጢት ክልከላን ለማሳካት ህብረተሰቡ እያደረገ ያለው ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
Feb 27, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ህብረተሰቡ የፕላስቲክ ከረጢቶች ላይ የተጣለውን ክልከላ ተግባራዊ ለማድረግ እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ አጠናክሮ እንዲቀጥል የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። ባለስልጣኑ ከአምራቾች ጋር በመሆን ተኪ ምርቶች በስፋት ለተጠቃሚ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በሀዋሳ በፕላስቲክ ከረጢት ምትክ አማራጭ ምርቶችን የመጠቀም ልምድ እየዳበረ ነው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ 1383/2017 ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የፕላስቲክ ከረጢት ማምረት፣ ወደ ሃገር ማስገባት፣ መሸጥና መጠቀም ላይ ሙሉ ክልከላ ማድረጉ ይታወቃል። የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ አዋጁ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ቁጥር፣ የከተሞች መስፋፋት እንዲሁም የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስርዓት መዘርጋትን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ ነው። በለውጡ ዓመታት የተሰሩ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ፅዳት ማዕከል ያደረጉ እንዲሆኑ በማስቻል ንፁህና ፅዱ ለማድረግ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ አዋጅ ማዘጋጀት ማስፈለጉን ተናግረዋል። አዋጁ ለአንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ከረጢቶች(በተለምዶ ፌስታል የሚባሉት) ላይ ሙሉ በሙሉ ክልከላ ያደረገ አዋጅ መሆኑን አንስተዋል። አዋጁ የበርካታ ሀገራት ልምድን ከመቀመር ባለፈ የፕላስቲክ ከረጢቶች በጤና ላይ የሚያደርሱትን አሉታዊ ተፅዕኖ ታሳቢ በማድረግ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እነዚህ ፕላስቲክ ከረጢቶች ለካንሰር፣ ለአዕምሮ እድገት ውስንነት እና ለመተንፈሻ አካላት ህመሞች ምክንያት መሆናቸውን አንስተው፤ የአፈር ለምነትን፣ ውሃ አየር እና በእንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ እንደሆነ እንዲሁም የምግብ ዋስትናንና ሉዓላዊነትንም እንደሚያደናቅፍ አመልክተዋል። የፕላስቲክ ከረጢት አጠቃቀም ልምድን ለመቀየር ለአንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውሉ ፕላስቲክ ከረጢቶች ሙሉ በሙሉ መከልከላቸውን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅትም በአብዛኞቹ የሀገሪቷ አካባቢዎች ሕጉ ተፈፃሚ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጥብቅ የክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የአዋጁ ትግበራ የጊዜ ገደብ ተራዝሟል የሚል ሃሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ህብረተሰቡ በዚህ የተሳሳተ መረጃ ሳይዘናጋ ለአዋጁ ተፈፃሚነት የበኩሉን ሚና መወጣቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። ባለስልጣኑ ከአምራቾች ጋር በመሆን አማራጭ ምርቶች በስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ እየሰራ መሆኑን አንስተው፤ በዚህም አብዛኛው ኢንዱስትሪዎች ምርቶችን በስፋት እያመረቱ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አሁንም ምርትን በስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ መስራት እንደሚጠይቅ ጨምረው አስታውቀዋል። በአካባቢ ላይ የሚደርሱ ብክለቶች ዙሪያ ጥቆማ የሚያደርሱበት እንዲሁም ቅሬታ የሚያቀርቡበት የዲጂታል ስርዓት ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር እየተዘረጋ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በክልሉ በተያዘው የበጋ ወራት ከ64 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የአፈርና የውሃ ጥበቃ የተፋሰስ ልማት እየተከናወነ ነው
Feb 27, 2026 82
ጋምቤላ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በተያዘው የበጋ ወራት ከ64 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የአፈርና የውሃ ጥበቃ የተፋሰስ ልማት በመከናወን ላይ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮ ኃላፊው አድሮው ቱት ለኢዜአ እንደገለጹት ምርታማነትን ለማሳድግ በበጋው ወራት የተጠናከረ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በክልሉ በሚገኙ ሶስቱም ዞኖች የአፈርና ውሃ ጥበቃ የተፋስ ልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የተፋሰስ ልማት ስራዎች በክልሉ በሚገኙ 13 ወረዳዎች በተመረጡ 101 ተፋሰሶች በመደበኛና በፕሮጀክቶች ከ64ሺህ ሄክታር በላይ በሚሸፍን መሬት ላይ እየተከወነ መሆኑን ተናግረዋል። በተፋሰስ ልማት ስራው ከአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች በተጓዳኝ ባለፈው ክረምትና ከዚያ በፊት በአረንጓዴ አሻራ ልማት ለተተከሉ ችግኞች እንክብካቤ እየተደረገ እንደሆነም አክለዋል። በክልሉ በበጋው ወራት እየተካሄደ ያለውን የአፈርና ውሃ ጥበቃ የተፋሰስ ልማት ስራዎች በመጪው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስነ-ህይወት ለማላበስ በ66 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች የማፍላት ስራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በመጪው ክረምት በሚከናወነው ለአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር ከሚዘጋጁት ችግኞች መካከል ከ8 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ከደንነት በተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።
የመሬት እንቅስቃሴ አደጋዎችን ለመቀነስ የመከታተያ ማዕከላት ማስፋፋት ያስፈልጋል - የዘርፉ ምሁራን
Feb 26, 2026 132
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ የመሬትመንቀጥቀጥና የእሳተ ገሞራ አደጋዎችን ለመቀነስ የመከታተያ ማዕከላት ማስፋትና የህዝብን ግንዛቤ ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ "የመሬት መንቀጥቀጥና የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ አደጋ በኢትዮጵያ ስጋትና መፍትሔዎች" በሚል መሪ ሃሳብ የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው። በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በተሰናዳው መድረክ የታደሙት የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ተከተል ዮሀንስ፤ ምሁራን በሀገራቸው ጉዳይ ያላቸውን ሚና ማላቅ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በተለያዩ ሀገራዊ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ጥናትና ምርምር በማካሄድ ለሕትመትና ተደራሽነት እንዲበቁ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በኢትዮጵያ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚኖራቸውን መፍትሔ አመላካች የጥናትና ምርምር ሥራ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የጂኦ-ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ ተመራማሪ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ፤ የመሬት እንቅስቃሴ በተፈጥሮ ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል ብለዋል። በመሬትና በብዝኅ ህይወት ላይ የሚፈጥረው የገጽታ ለውጥም በህዝብ ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ አኗኗር ሥርዓት ከፍተኛ ጫና እንደሚያሳድር ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የሚከሰቱ የመሬት እንቅስቃሴዎችንም በመከታተል በተለያዩ ጊዜያት ህዝቡን የማስገንዘብ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት መንቀጥቀጥና የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ አደጋዎችን አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠትም የማዕከላትን መረጃ ማጠናቀር አቅም ማጎልበት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። የምህንድስና የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡት የጂኦቴክኒክ ኢንጅነሪንግ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አስራት ወርቁ በበኩላቸው፤ የመሬት እንቅስቃሴ አደጋዎችን ለመቀነስ የግንባታ ጥራትን ማስጠበቅ ይገባል ብለዋል። የህንፃና ተያያዥ መሰረተ ልማት ገንቢ ተቋማትና መሃንዲሶችም ከመሬት ሳይንስ ተመራማሪዎች ጋር በመቀናጀት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የመሬት መንቀጥቀጥ ማህበራዊ ገጽታን አስመልክቶ ጽሁፍ ያቀረቡት ፕሮፌሰር ተገኝ ገብረእግዚአብሔር፤ የስምጥ ሸለቆ የከተሜነት መስፋፋት ለመሬት እንቅስቃሴ አደጋ ተጋላጭነትን ከፍ ያደርጋል ብለዋል። ለዚህም የሀገራትን ተሞክሮ በመቀመር የቅድመ ማስጠንቀቂያና የመሠረተ ልማት ጥራትን ማጠናከር እንደሚገባ አስረድተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የኢጋድ እና ተመድ ትብብር ለቀጣናዊ ሰላም
Feb 26, 2026 117
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ያላቸውን የጋራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የኢጋድ የደቡብ ሱዳን ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሙሳ ጃማ አሊ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። ልዩ ልዑኮቹ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት በተለይም በደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት የአምስት አባል ሀገራት ኮሚቴ (AU C5) እና ኢጋድ ያደረጉት የጋራ ጉባኤ የተገኙ ውጤቶች ላይም መክረዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ሰላም፣ መረጋጋት እና ቀጣናዊ ትብብር እውን እንዲሆን ያላቸውን ቅንጅት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ሩሲያ በትብብር መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
Feb 24, 2026 198
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ሩሲያ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ አጋርነት ዳይሬክተር ታትያና ዶቭጋሌንኮ ጋር በተቋሙ መቀመጫ ጅቡቲ ተወያይተዋል። በውይይቱ ወቅት ኢጋድ እና ሩሲያ በፖሊሲና ደኅንነት፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ ሳይንስ እና ትምህርት ዘርፎች ትብብር ማጎልበት የሚያስችላቸውን ስምምነት እና የድርጊት መርሐ-ግብር ተፈራርመዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ ጉዳዮች ተቀራርበው ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Feb 23, 2026 141
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ በሰላም፣ ልማት እና ዲፕሎማሲ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ(ኢ/ር) ከተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አፍሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ ለረጅም ጊዜ የቆየ እና ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው ትብብሩ በጥልቅ የባህል፣ የኢኮኖሚና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ላይ የተመሰረተ መሆኑን አውስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ በአፍሪካ ያላትን ዘላቂ ትብብር እና በአህጉሪቱ እያደገ የመጣውን ኢንቨስትመንት አልፎም በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ያላትን ገንቢ ሚና አድንቀዋል። ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመቀናጀት በሊቢያ፣ ሱዳን እና ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች እያሳየች ያለውን የዲፕሎማሲ ድጋፍ እና ተሳትፎ አዎንታዊ መሆኑን አመልክተዋል። የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ በበኩላቸው የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ በልማት፣ በሰላም እና በባለብዙ ወገን ትብብር ያለውን የመሪነት ሚና አንስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ልማት፣ ሰላም፣ ደህንነት እና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላትን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የአፍሪካ ህብረትና ሳዑዲ አረቢያ ያላቸውን ግንኙነት በጋራ መከባበር መንፈስ፣ በወዳጅነት እና በስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ በመመስረት የበለጠ ለማጠናከር የጋራ ፍላጎት ማሳየታቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና የፈጠረውን የንግድ ትስስር ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 206
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን የንግድ ትስስር ዕድል በአግባቡ ለመጠቀም በመንግሥታትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለ አጋርነትን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የስምምነቱ ትግበራ የንግድ መሰናክሎችን በማስቀረት የሀገራትን የንግድ ልውውጥ ለማሳለጥ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ ነው። እስካሁን 50 ሀገራት ፈርመው ያጸደቁት ይህ የንግድ ቀጣና፤ በዲጂታል የኢኮኖሚ ዕድገት የፋይናንስ ቴክኖሎጂን በማስፋት የአኅጉሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በማዘመንና የገንዘብ ዝውውርን በማቀላጠፍ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት የአሰራር ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተዳራሽ ለማድረግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ዘርግቷል የኢትዮጵያ ቱሪዝም አዲሱ ገጽታ፤ ከአማራጭ ማጣት ወደ መዳረሻዎች ብዛት በኢትዮጵያ ለግል ዘርፉ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ኢኮኖሚው እየተነቃቃ ነው የአፍሪካን የተፈጥሮ ሃብትም በተሻለ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነት በማልማት የመሰረተ ልማት፣ የዋጋ ግሽበትና የንግድ መሰናክሎችን ለመቀነስ አይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም አስረድተዋል። በዚህም አባል ሀገራት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን በማፋጠን የእርስበርስ የንግድ ልውውጥን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን ዕድል ለመጠቀም የግሉ ዘርፍና የአባል ሀገራት መንግሥታት የእርስ በርስ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሰረትም የአባል ሀገራት ኢንቨስትመንትን የሚያነቃቃ የኢንቨስትመንት ጥበቃ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስረድተዋል። የስምምነቱ የኢንቨስትመንት ጥበቃም የአፍሪካን በመተማመን ላይ የተመሰረተ የእርስበርስ ንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን አስታውቀዋል።
ሐተታዎች
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 188
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 208
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 655
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 989
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 209
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 315
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1067
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1035
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3543
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2361
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8156
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6639
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 270
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 276
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።