ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በአፍሪካ ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ አንጎላን አሸነፈች
Dec 22, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት የመጀመሪያ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ አንጎላን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ማምሻውን በማራካሽ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኦስዊን አፖሊስ እና ላይል ፎስተር የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ማኑኤል ሉዊስ ዳ ሲልቫ ካፉማና (በቅጽል ስሙ ሾው) ለአንጎላ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጨዋታው ተመጣጣኝ እና አዝናኝ ፉክክር ተደርጎበታል። ውጤቱን ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ ምድብ ሁለትን በሶስት ነጥብ መምራት ጀምራለች። በዚሁ ምድብ ምሽት አምስት ላይ ግብጽ ከዚምባቡዌ በአጋዲር ስታዲየም ይጫወታሉ።
የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም አለባቸው
Dec 22, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ በሥራዎቻቸው ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የሰላም ግንባታ የእያንዳንዱ ተቋም ኃላፊነት ነው፡፡ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን በመግለጽ፤ ሁሉም አካል ሰላምን የእለት ተዕለት እንቅስቃሴው ዕቅድ አካል ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ የሰላም ግንባታ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት አለበት ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር) ተቋማት ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ተቋማት ግጭትን መከላከልና ማስቀረት የሚያስችል የሰላም ዕቅድ የሥራቸው አካል መሆን አለበት ብለዋል፡፡ በዚህም ከፌደራል እስከ ቀበሌ ያሉ የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡ፣ ሲተገብሩና ክትትል ሲያደርጉ ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
በላሊበላ የሚከበረው የገና በዓል በአማራ ክልል ለሚታየው የቱሪዝም መነቃቃት ጉልህ አስተዋጽኦ ያደርጋል
Dec 22, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 13/2018 (ኢዜአ)፡- በላሊበላ ከተማ በድምቀት የሚከበረው የገና በዓል ለአማራ ክልል የቱሪዝም እንቅስቃሴ መነቃቃት ከፍተኛ ሚና እንዳለው የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። ላሊበላ ዓለም አቀፍ የቱሪስት መዳረሻ ከመሆኑ ባለፈ የገና በዓል በድምቀት ስለሚከበርበት በርካታ ቱሪስቶች በተለያዩ የመጓጓዣ አማራጮች ወደ ሥፍራው እንደሚመጡ የቢሮ ኃላፊ መልካሙ ፀጋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል። ቱሪስቱም የተቀናጀ የቱሪዝም አገልግሎትን መሰረት አድርጎ ስለሚመጣ ላሊበላን ብቻ ሳይሆን፤ ሌሎች መዳረሻዎችን አሥተሣሥሮ እንደሚጎበኝም ጠቁመዋል። ይህም እንደ ክልል ያለውን የቱሪዝም ዘርፍ እንዲነቃቃ ያደርገዋል ነው ያሉት ኃላፊው። ክልሉ በባህል፣ በቅርስ፣ በእንግዳ ተቀባይነትና በሌሎች ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ድንቅ ምድር መሆኑን ጠቁመው፤ ሕዝቡ በሚታወቅበት እንግዳ ተቀባይነት ባህሉ ለጎብኚዎች አቀባበል እንዲያደርግም ጠይቀዋል። የክልሉ መንግስትም በዓሉ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር እና ለእንግዶቹም ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የላሊበላ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ መሳይ ወዳጆ በበኩላቸው፤ ከቱሪዝም ጋር የተሣሠረውን የከተማዋን ኢኮኖሚ በይበልጥ በማነቃቃት ረገድ የገና በዓል ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ኢኮኖሚው ከቱሪዝም ጋር መቆራኘቱን የተገነዘበው የከተማዋ ነዋሪም፤ የአካባቢውን ሰላም በማጽናት ለእንግዶች ምቹ አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅቷል ብለዋል።
በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Dec 22, 2025 54
ጋምቤላ፤ ታህሳስ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በወቅታዊ የፀጥታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ ውይይት አድርገዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ ሰላምን ለማወክና ልማትን ለማደናቀፍ እኩይ አላማ ይዘው የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውን ገልጸዋል። በተለይም የፀጥታ ችግር እንዲከሰትና የልማት ስራዎች እንዲስተጓጎሉ ጥረት ማድረጋቸውን አንስተው በህዝቡና የጸጥታ ሃይሉ ትብብር የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰላም የማስጠበቅና ልማትን የማስቀጠል ስራ በልዩ ትኩረት የሚከናወን መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ጥረት ውስጥ የህዝቡ ትብብር አበረታች መሆኑን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የጥፋት ቡድኖችን እኩይ አላማ በማክሸፍ ለክልሉ ሰላምና ልማት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ማሊ እና ዛምቢያ አቻ ተለያዩ
Dec 22, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ ሁለተኛ ጨዋታ ማሊ እና ዛምቢያ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በመሐመድ አምስተኛ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ላሲን ሲናዮኮ በ61ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ማሊን መሪ ሆና ነበር። ይሁንና ፓትሰን ዳካ በ92ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ግብ ለዛምቢያ ወሳኝ አንድ ነጥብ አስገኝታለች። ማሊ በ41ኛው ደቂቃ ያገኘችውን ፍጹም ቅጣት ምት ኤል ቢላል ቱሬ አምክኖታል። ውጤቱን ተከትሎ ማሊ እና ዛምቢያ በውድድሩ የመጀመሪያ ነጥባቸውን አግኝተዋል። በምድብ አንድ ትናንት አዘጋጇ ሞሮኮ ኮሞሮስን 2 ለ 0 በማሸነፍ በሶስት ነጥብ ምድቡን እየመራች ነው።
ፖለቲካ
የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም አለባቸው
Dec 22, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ በሥራዎቻቸው ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የሰላም ግንባታ የእያንዳንዱ ተቋም ኃላፊነት ነው፡፡ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን በመግለጽ፤ ሁሉም አካል ሰላምን የእለት ተዕለት እንቅስቃሴው ዕቅድ አካል ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ የሰላም ግንባታ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት አለበት ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር) ተቋማት ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ተቋማት ግጭትን መከላከልና ማስቀረት የሚያስችል የሰላም ዕቅድ የሥራቸው አካል መሆን አለበት ብለዋል፡፡ በዚህም ከፌደራል እስከ ቀበሌ ያሉ የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡ፣ ሲተገብሩና ክትትል ሲያደርጉ ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Dec 22, 2025 54
ጋምቤላ፤ ታህሳስ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በወቅታዊ የፀጥታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ ውይይት አድርገዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ ሰላምን ለማወክና ልማትን ለማደናቀፍ እኩይ አላማ ይዘው የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውን ገልጸዋል። በተለይም የፀጥታ ችግር እንዲከሰትና የልማት ስራዎች እንዲስተጓጎሉ ጥረት ማድረጋቸውን አንስተው በህዝቡና የጸጥታ ሃይሉ ትብብር የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰላም የማስጠበቅና ልማትን የማስቀጠል ስራ በልዩ ትኩረት የሚከናወን መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ጥረት ውስጥ የህዝቡ ትብብር አበረታች መሆኑን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የጥፋት ቡድኖችን እኩይ አላማ በማክሸፍ ለክልሉ ሰላምና ልማት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ተቋማት ሰላምን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለሰላም ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ አለባቸው
Dec 22, 2025 78
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ ተቋማት ሰላምን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለሰላም ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንደሚገባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ እና ሌሎችም የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና እንግዶች ተገኝተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት፤ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የሰላም ግንባታ ጉዳይ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት ይኖርበታል ብለዋል። ተቋማትም የሰላም ግንባታን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን አስቀምጠው መሄድ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ ተቋማት የግጭት መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮችን መከላከልና ማስቀረት በሚያስችል መንገድ መሥራት አለባቸው ብለዋል። እንዲሁም ህግና ስርዓትን ያልተከተሉ አካሄዶችን በማስተካከል፣ የፕሮጀክቶች አፈፃፀምን በማላቅ፣ አሳታፊነትን በማጎልበት ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምን ማፅናት እንደሚገባ ተናግረዋል። የግጭት ጥንስሶችን ከስር መሰረታቸው ለማጥፋት ተጠያቂነትን ማስፈን፣ ስራዎችን በጊዜና በጥራት ማጠናቀቅ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል። የተቋማት ስራዎች የግጭት መንስኤዎች መሆን የለባቸውም ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር)፤ ግጭትን መከላከልና ሰላም ግንባታ ላይ መሥራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የሰላም ግንባታ በግብርና በጤና እና በሌሎችም ተቋማት እንዴት ይካተት ለሚለው ራሱን የቻለ ሰነድ ሊዘጋጅለት ይገባል ብለዋል።
የሚሰጠንን ሀገራዊ ተልዕኮና ግዳጆች በጀግንነት ለመፈጸም ዝግጁ ነን - ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ አባላት
Dec 22, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ የሀገር ሰላምና የሕዝብ ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚሰጣቸውን ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነትና በሰብዓዊነት ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ አባላት ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ፖሊስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በፖሊስ አካዳሚው አቅም ያሰለጠናቸውን ልዩ የኮማንዶ ኃይል አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በትናንትናው ዕለት በአዋሽ የስልጠና ማዕከል አስመርቋል። ልዩ የኮማንዶ ኃይሉ ልዩ እና አስቸጋሪ ኦፕሬሽኖችን በእውቀትና በጀግንነት የሚፈጽም መሆኑም በዚሁ ወቅት ተጠቁሟል፡፡ ተመራቂ የኮማንዶ አባላቱ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በጀግንነትና በሰብዓዊነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ኮንስታብል ሚኪያስ ገበያው በሰጠው አስተያየት የወሰዱት ስልጠና የአካል ብቃት ብቻ ሳይሆን የአእምሮ ጽናትና ልዩ የኦፕሬሽን ጥበቦችን ያስጨበጣቸው መሆኑን ገልጿል። በዚህም የሚሰጠውን ማንኛውንም ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ሀገርና ህዝብን ከማንኛውም የጥፋት ኃይል የመጠበቅና የሕዝብን ሰላም ለማስጠበቅ እስከ መስዋዕትነት ጭምር ለመክፈል ዝግጁ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡ ሌላኛዋ ተመራቂ ኮንስታብል ምርትነሽ ተካ በሰጠችው አስተያየት የስልጠናው ሂደት ገንቢ፣ አስተማሪና ለቀጣይ ተልዕኮ እንዲዘጋጁ የሚያደርግ መሆኑን ተናግራለች፡፡ ባገኘችው ስልጠና የሚሰጣትን ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኗንም ገልጻለች፡፡ ኮንስታብል አብዲ ተረፈ በበኩሉ ኢትዮጵያን ከውጪ ባዳ እና ከውስጥ ባንዳ ለመጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ዳር ድንበር ለማስከበር የፈጸሙትን ገድል በጀግንነት ለመድገም መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የእነሱን ፈለግ በመከተል ሀገራቸውን ለማገልገል መዘጋጀት እንደሚገባቸው ተመራቂዎቹ ጠቁመዋል፡፡ ተመራቂዎቹ ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተውጣጥተው በጋራ ያሳለፉት የስልጠና ጊዜ የኢትዮጵያን አንድነት በተግባር ያዩበት መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኤሊት ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው
Dec 21, 2025 157
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 12/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተልዕኮው ልዩና ስትራቴጂያዊ የሆነ ኤሊት ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ዛሬ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አካዳሚ በራሱ አቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ ፖሊስ አባላት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በመገኘቴና ይህንን ጀግና የፖሊስ ሠራዊት በመመልከቴ የተሰማኝ ደስታ ላቅ ያለ ነው ብለዋል። መንግሥታችን በፀጥታ ዘርፉ ባከናወነው መጠነ-ሰፊ ሪፎርም፤ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ ለሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ ጠንካራ ዘብ፣ በሙያው ብቁና በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ በሕዝብ ፍቅርና አመኔታ የተገነባ ፕሮፌሽናል ተቋም ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኤሊት የፖሊስ ሠራዊት ማንኛውንም ውስብስብና አስቸጋሪ የጸጥታ ስጋቶችን በአጭር ጊዜና በከፍተኛ ብቃት የመቀልበስ ልዩ አቅም እንዳለውም ጠቁመዋል። የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የሕዝባችንን ሰላም የሚፈታተኑ የሽብርና የከባድ ወንጀል ሙከራዎችን በብቃት የመከላከልና መቆጣጠር ኃላፊነት ተጥሎበታል ሲሉም አስታውቀዋል። ሀገራችን በሁሉም መስክ ለምታስመዘግበው ድል ዋነኛው መሠረት ሰላምና ፀጥታ ነው ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመልዕክታቸው። ለዚህ ሰላም ሲሉ ሕይወታቸውን እስከመስጠት የደረሰ መስዋዕትነት ለከፈሉና ሀገርን ለማጽናት በቁርጠኝነት ለቆሙ የፖሊስ አባሎቻችን ትልቅ ክብር እንደሚገባቸውም ነው ያስገነዘቡት። የእስካሁኑ ስኬት ይበልጥ ለሥራ የሚያተጋ መሆኑንም አመላክተዋል። በመጪው ግንቦት የሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነፃ ሆኖ እንዲከናወን እንደ COP32 ያሉ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ መድረኮች እንዲሁም ደማቅ የአደባባይ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቁ የፌዴራል ፖሊስ ኃይላችን የተጣለበትን ታሪካዊ አደራ በብቃት እንደሚወጣ ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል። የዛሬ ተመራቂ የኤሊት ፖሊስ ሠራዊት አባላት የኢትዮጵያ ሕዝቦች ኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ሉዓላዊነት ምልክት ናችሁ ሲሉም አስረድተዋል። ሀገርንና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከየትኛውም አደጋ የመከላከል ኃላፊነታችሁን በታማኝነት እንድትወጡ አደራ ማለት እፈልጋለሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ልዩ የኮማንዶ ኃይላችን ልዩ እና አስቸጋሪ ኦፕሬሽኖችን በእውቀትና በጀግንነት የሚፈጽም ነው
Dec 21, 2025 165
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 12/2018(ኢዜአ)፦ ልዩ የኮማንዶ ኃይላችን ልዩ እና አስቸጋሪ ኦፕሬሽኖችን በእውቀትና በጀግንነት የሚፈጽም ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በአካዳሚው ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን ልዩ የኮማንዶ አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ዛሬ በአዋሽ የማሰልጠኛ ማዕከል አስመርቋል። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ተመራቂዎቹ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተመለመሉ ሲሆኑ፤ ላለፉት 16 ወራት ልዩ ፖሊሳዊ ስልጠና ወስደዋል። በዚህ ልዩ የኮማንዶ ስልጠና ማናቸውንም ልዩ ኦፕሬሽኖች እና ግዳጆች መወጣት የሚያስችል ጠንካራ አቅም መፍጠራቸውንም ጠቅሰዋል። ፖሊስ በሕግ፣ በአሠራር፣ በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በውስጥና በውጪ ግንኙነት ስኬታማ ሪፎርም ማካሄዱን አንስተዋል። በዚህም የሀገር አለኝታ የሆነ፣ ገለልተኛና ሙያዊ ብቃት እና የመፈጸም አቅም ያለው፣ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የፖሊስ ተቋም መገንባቱን ገልጸዋል። በተለይም በከፍተኛ ትኩረት ከተሠሩ ተግባራት መካከል የሰው ኃይሉ ወቅቱ የሚፈልገውን የተሟላ ፖሊሳዊ እውቀት፣ ክህሎት እና ስብዕና እንዲላበስ የፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋማትን ማሳደግ ችለናል ነው ያሉት። የፖሊስ ኃይሉ ባለፉት ጊዜያት በሀገር እና በሕዝቦቿ ላይ በባንዳ እና በባዳ የተቃጡ ሀገር የማፍረስ ሴራዎችን ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር መስዋዕትነት በመክፈል ጭምር ማክሸፉንና ሰላምን ማረጋገጡን ገልጸዋል። ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ሰላምን ለማደናቀፍ የማይተኙ መሆናቸውን አመልክተው፤ ማናቸውንም ሀገራዊ ግዳጆች በብቃት እና በቁርጠኝነት ለመወጣት ሁሌም ዝግጁ ነን ብለዋል። ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በስኬት ለማጠናቀቅ የፖሊስ ኃይሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀቱን አረጋግጠዋል። የልዩ ኮማንዶ ኃይል ተልዕኮ ብርታትን፣ ትዕግስትን፣ የመንፈስ ጽናትን፣ እምነትንና መስዋዕትነትን የሚጠይቅ መሆኑን አንስተዋል። የተልዕኮውን ክብደት በአግባቡ በመገንዘብ በስልጠና ወቅት ባሳዩት ብቃት፣ የአዕምሮ ጽናት፣ እውቀትና ክህሎት ሙያቸውን በብቃትና በቁርጠኝነት በተግባር እንዲወጡም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያ ለሁሉም ዓይነት ፈተናዎች ሁሌም ዝግጁ የሆነ የፀጥታ ኃይል ገንብታለች
Dec 21, 2025 185
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 12/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለሁሉም ዓይነት ፈተናዎች ሁሌም ዝግጁ የሆነ የፀጥታ ኃይል መገንባቷን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ፖሊስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በፖሊስ አካዳሚው አቅም ያሰለጠናቸውን ልዩ የኮማንዶ ኃይል አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ዛሬ በአዋሽ የስልጠና ማዕከል አስመርቋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የለውጡ መንግሥት ውጤታማ ከሆነባቸው የሪፎርም ሥራዎች አንዱ በፀጥታ ተቋማት ላይ ተግባራዊ የሆነው ሪፎርም መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሪፎርም የፀጥታ ተቋማት ንቁ፣ ብቁና ቴክኖሎጂ የታጠቁ እንዲሆኑ ማስቻሉን ተናግረዋል። በስልጠና እና በአደረጃጀት የተሻለ ሂደት ተጉዘናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ ለሁሉም ዓይነት ፈተናዎች ሁሌም ዝግጁ የሆነ ኃይል እንዲኖራት አድርገናል ብለዋል። ዛሬ የተመረቁት ልዩ ኮማንዶዎችም የዚህ ውጤት ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በሪፎርሙ መሠረት የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ጠበቃ የሆነ፣ በሙያው የሚኮራ፣ ሕጎችን በአግባቡ በመተግበር በሕዝብ ፍቅርና አመኔታ ያለው ጠንካራና በቴክኖሎጂ የተደራጀ ተቋም እየገነባ እንደሚገኝም አንስተዋል። የፌዴራል ፖሊስ የሪፎርም አካል የሆነውን ልዩ የኮማንዶ ፖሊስ ለመጀመሪያ ጊዜ በራስ አቅም አሰልጥኖ በዛሬው ዕለት ማስመረቁም የተቋማዊ አቅሙ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ ኃይል የትኛውንም ወንጀል በመከላከልና የሀገርን ብልጽግና የማሳካት ብቃት ያለው ነው ብለዋል። በቀጣይ ከሀገራችን ዕድገት ጋር የተጣጣመ የኢትዮጵያን ከፍታ የሚመጥን የፖሊስ ተቋም ግንባታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መንግሥት አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የዛሬ ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ ፖሊስ አባላት የኢትዮጵያን አንድነትና ሉዓላዊነት ማረጋገጫ የሆነውን ሕገ መንግሥት የማክበር እና የማስከበር ከፍተኛ ኃላፊነት አለባችሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በመደመር የሚመራው ፖሊስ ሕዝብን ያከብራል፣ ያገለግላል፣ ይጠብቃል፣ ለሕዝብም መስዋዕትነት ይከፍላል ብለዋል። ከነገዋ የበለፀገች ኢትዮጵያ ተጠቃሚ ለመሆን ብልጽግናን የሚያሳልጥ ኃይል ሆኖ መገኘት እንደሚገባ ጠቅሰው፤ ይህም ዛሬ የተመረቁ የፖሊስ አባላት ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል። የልዩ ኮማንዶ ፖሊስ ተመራቂዎች የቀሰሙትን የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና በተገቢው መንገድ በመጠቀም ሕዝብንና ሀገርን በቅንነት፣ በታማኝነትና በጀግንነት እንዲያገለግሉም አሳስበዋል።
በትግራይ ክልል ሰላም ለማስፈን የሚከናወኑ ተግባራትን የሚያደናቅፉ አካላትን ህብረተሰቡ አጥብቆ መታገል አለበት
Dec 21, 2025 136
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 12/2018(ኢዜአ)፦ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ሰላም ለመስፈን የሚያከናውናቸውን ተግባራት የሚያደናቅፉ አካላትን ህብረተሰቡ አጥብቆ ሊታገላቸው እንደሚገባ ስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ገለጸ። የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ አባል ጣዕመ አራዶም ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም እንዳይሰፍንና የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዳይተገበር እንቅፋት የሚፈጥሩ አካላትን የክልሉ ህዝብ በፅናት ሊታገላቸው እንደሚገባ ገልጸዋል። የፌዴራል መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነትን ተከትሎ በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ልማት እንዲመጣ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በተለይም ለክልሉ አስፈላጊውን የልማት በጀት መመደቡ፣ የባንክ፣ የጤና እና የማህበራዊ አገልግሎቶች ዳግም እንዲጀመሩ ማድረጉ፣ የፈረሱ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን መልሶ መገንባቱን አውስተው፤ ተፈናቃዮችን ወደ ቀድሞ ቀያቸው በመመለስ ረገድ የፌዴራል መንግስት ላከናወናቸው ተግባራት አድናቆት እንዳላቸውም ተናግረዋል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሉ የሚንቀሳቀሰው ቡድን መንግስት ተፈናቃዮችን ለመመለስና ሰላም ለማስፈን የሚያደርገውን ጥረት እያደናቀፈ እንደሚገኝ አንስተዋል። ይህ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት ወደ ኋላ የሚጎትት መሆኑን ገልጸው፤ ህብረተሰቡ እነዚህን እንቅፋቶች በትጋት እንዲታገል ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል። ስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመጪው ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ሙሉ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ያስታወቁት አቶ ጣዕመ፤ የእጩዎች ምልመላና አስፈላጊ የሆኑ የቅድመ-ምርጫ ሂደቶች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። ምርጫው መካሄዱ የትግራይ ህዝብ በሀገሪቱ የፖለቲካ መድረክ ተገቢውን ውክልና ማግኘት እንደሚያስችለውም ነው የገለጹት። የክልሉ ህዝብ እንደ ሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ሁሉ በዴሞክራሲ፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ የሚሆነው በምርጫ የህዝብ ውክልና ሲረጋገጥ ብቻ እንደሆነም አስታውቀዋል። የፌዴራል መንግስት በአካባቢው ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት እስካሁን የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥልም ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል።
ፖለቲካ
የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም አለባቸው
Dec 22, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ በሥራዎቻቸው ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የሰላም ግንባታ የእያንዳንዱ ተቋም ኃላፊነት ነው፡፡ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን በመግለጽ፤ ሁሉም አካል ሰላምን የእለት ተዕለት እንቅስቃሴው ዕቅድ አካል ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ የሰላም ግንባታ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት አለበት ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር) ተቋማት ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ተቋማት ግጭትን መከላከልና ማስቀረት የሚያስችል የሰላም ዕቅድ የሥራቸው አካል መሆን አለበት ብለዋል፡፡ በዚህም ከፌደራል እስከ ቀበሌ ያሉ የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡ፣ ሲተገብሩና ክትትል ሲያደርጉ ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Dec 22, 2025 54
ጋምቤላ፤ ታህሳስ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በወቅታዊ የፀጥታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ ውይይት አድርገዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ ሰላምን ለማወክና ልማትን ለማደናቀፍ እኩይ አላማ ይዘው የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውን ገልጸዋል። በተለይም የፀጥታ ችግር እንዲከሰትና የልማት ስራዎች እንዲስተጓጎሉ ጥረት ማድረጋቸውን አንስተው በህዝቡና የጸጥታ ሃይሉ ትብብር የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰላም የማስጠበቅና ልማትን የማስቀጠል ስራ በልዩ ትኩረት የሚከናወን መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ጥረት ውስጥ የህዝቡ ትብብር አበረታች መሆኑን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የጥፋት ቡድኖችን እኩይ አላማ በማክሸፍ ለክልሉ ሰላምና ልማት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ተቋማት ሰላምን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለሰላም ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ አለባቸው
Dec 22, 2025 78
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ ተቋማት ሰላምን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለሰላም ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንደሚገባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ እና ሌሎችም የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና እንግዶች ተገኝተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት፤ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የሰላም ግንባታ ጉዳይ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት ይኖርበታል ብለዋል። ተቋማትም የሰላም ግንባታን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን አስቀምጠው መሄድ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ ተቋማት የግጭት መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮችን መከላከልና ማስቀረት በሚያስችል መንገድ መሥራት አለባቸው ብለዋል። እንዲሁም ህግና ስርዓትን ያልተከተሉ አካሄዶችን በማስተካከል፣ የፕሮጀክቶች አፈፃፀምን በማላቅ፣ አሳታፊነትን በማጎልበት ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምን ማፅናት እንደሚገባ ተናግረዋል። የግጭት ጥንስሶችን ከስር መሰረታቸው ለማጥፋት ተጠያቂነትን ማስፈን፣ ስራዎችን በጊዜና በጥራት ማጠናቀቅ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል። የተቋማት ስራዎች የግጭት መንስኤዎች መሆን የለባቸውም ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር)፤ ግጭትን መከላከልና ሰላም ግንባታ ላይ መሥራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የሰላም ግንባታ በግብርና በጤና እና በሌሎችም ተቋማት እንዴት ይካተት ለሚለው ራሱን የቻለ ሰነድ ሊዘጋጅለት ይገባል ብለዋል።
የሚሰጠንን ሀገራዊ ተልዕኮና ግዳጆች በጀግንነት ለመፈጸም ዝግጁ ነን - ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ አባላት
Dec 22, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ የሀገር ሰላምና የሕዝብ ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚሰጣቸውን ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነትና በሰብዓዊነት ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ አባላት ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ፖሊስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በፖሊስ አካዳሚው አቅም ያሰለጠናቸውን ልዩ የኮማንዶ ኃይል አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በትናንትናው ዕለት በአዋሽ የስልጠና ማዕከል አስመርቋል። ልዩ የኮማንዶ ኃይሉ ልዩ እና አስቸጋሪ ኦፕሬሽኖችን በእውቀትና በጀግንነት የሚፈጽም መሆኑም በዚሁ ወቅት ተጠቁሟል፡፡ ተመራቂ የኮማንዶ አባላቱ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በጀግንነትና በሰብዓዊነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ኮንስታብል ሚኪያስ ገበያው በሰጠው አስተያየት የወሰዱት ስልጠና የአካል ብቃት ብቻ ሳይሆን የአእምሮ ጽናትና ልዩ የኦፕሬሽን ጥበቦችን ያስጨበጣቸው መሆኑን ገልጿል። በዚህም የሚሰጠውን ማንኛውንም ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ሀገርና ህዝብን ከማንኛውም የጥፋት ኃይል የመጠበቅና የሕዝብን ሰላም ለማስጠበቅ እስከ መስዋዕትነት ጭምር ለመክፈል ዝግጁ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡ ሌላኛዋ ተመራቂ ኮንስታብል ምርትነሽ ተካ በሰጠችው አስተያየት የስልጠናው ሂደት ገንቢ፣ አስተማሪና ለቀጣይ ተልዕኮ እንዲዘጋጁ የሚያደርግ መሆኑን ተናግራለች፡፡ ባገኘችው ስልጠና የሚሰጣትን ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኗንም ገልጻለች፡፡ ኮንስታብል አብዲ ተረፈ በበኩሉ ኢትዮጵያን ከውጪ ባዳ እና ከውስጥ ባንዳ ለመጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ዳር ድንበር ለማስከበር የፈጸሙትን ገድል በጀግንነት ለመድገም መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የእነሱን ፈለግ በመከተል ሀገራቸውን ለማገልገል መዘጋጀት እንደሚገባቸው ተመራቂዎቹ ጠቁመዋል፡፡ ተመራቂዎቹ ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተውጣጥተው በጋራ ያሳለፉት የስልጠና ጊዜ የኢትዮጵያን አንድነት በተግባር ያዩበት መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኤሊት ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው
Dec 21, 2025 157
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 12/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተልዕኮው ልዩና ስትራቴጂያዊ የሆነ ኤሊት ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ዛሬ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አካዳሚ በራሱ አቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ ፖሊስ አባላት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በመገኘቴና ይህንን ጀግና የፖሊስ ሠራዊት በመመልከቴ የተሰማኝ ደስታ ላቅ ያለ ነው ብለዋል። መንግሥታችን በፀጥታ ዘርፉ ባከናወነው መጠነ-ሰፊ ሪፎርም፤ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ ለሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ ጠንካራ ዘብ፣ በሙያው ብቁና በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ በሕዝብ ፍቅርና አመኔታ የተገነባ ፕሮፌሽናል ተቋም ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኤሊት የፖሊስ ሠራዊት ማንኛውንም ውስብስብና አስቸጋሪ የጸጥታ ስጋቶችን በአጭር ጊዜና በከፍተኛ ብቃት የመቀልበስ ልዩ አቅም እንዳለውም ጠቁመዋል። የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የሕዝባችንን ሰላም የሚፈታተኑ የሽብርና የከባድ ወንጀል ሙከራዎችን በብቃት የመከላከልና መቆጣጠር ኃላፊነት ተጥሎበታል ሲሉም አስታውቀዋል። ሀገራችን በሁሉም መስክ ለምታስመዘግበው ድል ዋነኛው መሠረት ሰላምና ፀጥታ ነው ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመልዕክታቸው። ለዚህ ሰላም ሲሉ ሕይወታቸውን እስከመስጠት የደረሰ መስዋዕትነት ለከፈሉና ሀገርን ለማጽናት በቁርጠኝነት ለቆሙ የፖሊስ አባሎቻችን ትልቅ ክብር እንደሚገባቸውም ነው ያስገነዘቡት። የእስካሁኑ ስኬት ይበልጥ ለሥራ የሚያተጋ መሆኑንም አመላክተዋል። በመጪው ግንቦት የሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነፃ ሆኖ እንዲከናወን እንደ COP32 ያሉ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ መድረኮች እንዲሁም ደማቅ የአደባባይ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቁ የፌዴራል ፖሊስ ኃይላችን የተጣለበትን ታሪካዊ አደራ በብቃት እንደሚወጣ ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል። የዛሬ ተመራቂ የኤሊት ፖሊስ ሠራዊት አባላት የኢትዮጵያ ሕዝቦች ኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ሉዓላዊነት ምልክት ናችሁ ሲሉም አስረድተዋል። ሀገርንና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከየትኛውም አደጋ የመከላከል ኃላፊነታችሁን በታማኝነት እንድትወጡ አደራ ማለት እፈልጋለሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ልዩ የኮማንዶ ኃይላችን ልዩ እና አስቸጋሪ ኦፕሬሽኖችን በእውቀትና በጀግንነት የሚፈጽም ነው
Dec 21, 2025 165
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 12/2018(ኢዜአ)፦ ልዩ የኮማንዶ ኃይላችን ልዩ እና አስቸጋሪ ኦፕሬሽኖችን በእውቀትና በጀግንነት የሚፈጽም ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በአካዳሚው ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን ልዩ የኮማንዶ አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ዛሬ በአዋሽ የማሰልጠኛ ማዕከል አስመርቋል። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ተመራቂዎቹ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተመለመሉ ሲሆኑ፤ ላለፉት 16 ወራት ልዩ ፖሊሳዊ ስልጠና ወስደዋል። በዚህ ልዩ የኮማንዶ ስልጠና ማናቸውንም ልዩ ኦፕሬሽኖች እና ግዳጆች መወጣት የሚያስችል ጠንካራ አቅም መፍጠራቸውንም ጠቅሰዋል። ፖሊስ በሕግ፣ በአሠራር፣ በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በውስጥና በውጪ ግንኙነት ስኬታማ ሪፎርም ማካሄዱን አንስተዋል። በዚህም የሀገር አለኝታ የሆነ፣ ገለልተኛና ሙያዊ ብቃት እና የመፈጸም አቅም ያለው፣ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የፖሊስ ተቋም መገንባቱን ገልጸዋል። በተለይም በከፍተኛ ትኩረት ከተሠሩ ተግባራት መካከል የሰው ኃይሉ ወቅቱ የሚፈልገውን የተሟላ ፖሊሳዊ እውቀት፣ ክህሎት እና ስብዕና እንዲላበስ የፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋማትን ማሳደግ ችለናል ነው ያሉት። የፖሊስ ኃይሉ ባለፉት ጊዜያት በሀገር እና በሕዝቦቿ ላይ በባንዳ እና በባዳ የተቃጡ ሀገር የማፍረስ ሴራዎችን ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር መስዋዕትነት በመክፈል ጭምር ማክሸፉንና ሰላምን ማረጋገጡን ገልጸዋል። ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ሰላምን ለማደናቀፍ የማይተኙ መሆናቸውን አመልክተው፤ ማናቸውንም ሀገራዊ ግዳጆች በብቃት እና በቁርጠኝነት ለመወጣት ሁሌም ዝግጁ ነን ብለዋል። ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በስኬት ለማጠናቀቅ የፖሊስ ኃይሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀቱን አረጋግጠዋል። የልዩ ኮማንዶ ኃይል ተልዕኮ ብርታትን፣ ትዕግስትን፣ የመንፈስ ጽናትን፣ እምነትንና መስዋዕትነትን የሚጠይቅ መሆኑን አንስተዋል። የተልዕኮውን ክብደት በአግባቡ በመገንዘብ በስልጠና ወቅት ባሳዩት ብቃት፣ የአዕምሮ ጽናት፣ እውቀትና ክህሎት ሙያቸውን በብቃትና በቁርጠኝነት በተግባር እንዲወጡም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያ ለሁሉም ዓይነት ፈተናዎች ሁሌም ዝግጁ የሆነ የፀጥታ ኃይል ገንብታለች
Dec 21, 2025 185
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 12/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለሁሉም ዓይነት ፈተናዎች ሁሌም ዝግጁ የሆነ የፀጥታ ኃይል መገንባቷን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ፖሊስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በፖሊስ አካዳሚው አቅም ያሰለጠናቸውን ልዩ የኮማንዶ ኃይል አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ዛሬ በአዋሽ የስልጠና ማዕከል አስመርቋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የለውጡ መንግሥት ውጤታማ ከሆነባቸው የሪፎርም ሥራዎች አንዱ በፀጥታ ተቋማት ላይ ተግባራዊ የሆነው ሪፎርም መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሪፎርም የፀጥታ ተቋማት ንቁ፣ ብቁና ቴክኖሎጂ የታጠቁ እንዲሆኑ ማስቻሉን ተናግረዋል። በስልጠና እና በአደረጃጀት የተሻለ ሂደት ተጉዘናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ ለሁሉም ዓይነት ፈተናዎች ሁሌም ዝግጁ የሆነ ኃይል እንዲኖራት አድርገናል ብለዋል። ዛሬ የተመረቁት ልዩ ኮማንዶዎችም የዚህ ውጤት ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በሪፎርሙ መሠረት የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ጠበቃ የሆነ፣ በሙያው የሚኮራ፣ ሕጎችን በአግባቡ በመተግበር በሕዝብ ፍቅርና አመኔታ ያለው ጠንካራና በቴክኖሎጂ የተደራጀ ተቋም እየገነባ እንደሚገኝም አንስተዋል። የፌዴራል ፖሊስ የሪፎርም አካል የሆነውን ልዩ የኮማንዶ ፖሊስ ለመጀመሪያ ጊዜ በራስ አቅም አሰልጥኖ በዛሬው ዕለት ማስመረቁም የተቋማዊ አቅሙ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ ኃይል የትኛውንም ወንጀል በመከላከልና የሀገርን ብልጽግና የማሳካት ብቃት ያለው ነው ብለዋል። በቀጣይ ከሀገራችን ዕድገት ጋር የተጣጣመ የኢትዮጵያን ከፍታ የሚመጥን የፖሊስ ተቋም ግንባታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መንግሥት አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የዛሬ ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ ፖሊስ አባላት የኢትዮጵያን አንድነትና ሉዓላዊነት ማረጋገጫ የሆነውን ሕገ መንግሥት የማክበር እና የማስከበር ከፍተኛ ኃላፊነት አለባችሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በመደመር የሚመራው ፖሊስ ሕዝብን ያከብራል፣ ያገለግላል፣ ይጠብቃል፣ ለሕዝብም መስዋዕትነት ይከፍላል ብለዋል። ከነገዋ የበለፀገች ኢትዮጵያ ተጠቃሚ ለመሆን ብልጽግናን የሚያሳልጥ ኃይል ሆኖ መገኘት እንደሚገባ ጠቅሰው፤ ይህም ዛሬ የተመረቁ የፖሊስ አባላት ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል። የልዩ ኮማንዶ ፖሊስ ተመራቂዎች የቀሰሙትን የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና በተገቢው መንገድ በመጠቀም ሕዝብንና ሀገርን በቅንነት፣ በታማኝነትና በጀግንነት እንዲያገለግሉም አሳስበዋል።
በትግራይ ክልል ሰላም ለማስፈን የሚከናወኑ ተግባራትን የሚያደናቅፉ አካላትን ህብረተሰቡ አጥብቆ መታገል አለበት
Dec 21, 2025 136
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 12/2018(ኢዜአ)፦ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ሰላም ለመስፈን የሚያከናውናቸውን ተግባራት የሚያደናቅፉ አካላትን ህብረተሰቡ አጥብቆ ሊታገላቸው እንደሚገባ ስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ገለጸ። የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ አባል ጣዕመ አራዶም ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም እንዳይሰፍንና የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዳይተገበር እንቅፋት የሚፈጥሩ አካላትን የክልሉ ህዝብ በፅናት ሊታገላቸው እንደሚገባ ገልጸዋል። የፌዴራል መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነትን ተከትሎ በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ልማት እንዲመጣ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በተለይም ለክልሉ አስፈላጊውን የልማት በጀት መመደቡ፣ የባንክ፣ የጤና እና የማህበራዊ አገልግሎቶች ዳግም እንዲጀመሩ ማድረጉ፣ የፈረሱ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን መልሶ መገንባቱን አውስተው፤ ተፈናቃዮችን ወደ ቀድሞ ቀያቸው በመመለስ ረገድ የፌዴራል መንግስት ላከናወናቸው ተግባራት አድናቆት እንዳላቸውም ተናግረዋል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሉ የሚንቀሳቀሰው ቡድን መንግስት ተፈናቃዮችን ለመመለስና ሰላም ለማስፈን የሚያደርገውን ጥረት እያደናቀፈ እንደሚገኝ አንስተዋል። ይህ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት ወደ ኋላ የሚጎትት መሆኑን ገልጸው፤ ህብረተሰቡ እነዚህን እንቅፋቶች በትጋት እንዲታገል ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል። ስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመጪው ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ሙሉ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ያስታወቁት አቶ ጣዕመ፤ የእጩዎች ምልመላና አስፈላጊ የሆኑ የቅድመ-ምርጫ ሂደቶች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። ምርጫው መካሄዱ የትግራይ ህዝብ በሀገሪቱ የፖለቲካ መድረክ ተገቢውን ውክልና ማግኘት እንደሚያስችለውም ነው የገለጹት። የክልሉ ህዝብ እንደ ሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ሁሉ በዴሞክራሲ፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ የሚሆነው በምርጫ የህዝብ ውክልና ሲረጋገጥ ብቻ እንደሆነም አስታውቀዋል። የፌዴራል መንግስት በአካባቢው ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት እስካሁን የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥልም ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል።
ማህበራዊ
በላሊበላ የሚከበረው የገና በዓል በአማራ ክልል ለሚታየው የቱሪዝም መነቃቃት ጉልህ አስተዋጽኦ ያደርጋል
Dec 22, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 13/2018 (ኢዜአ)፡- በላሊበላ ከተማ በድምቀት የሚከበረው የገና በዓል ለአማራ ክልል የቱሪዝም እንቅስቃሴ መነቃቃት ከፍተኛ ሚና እንዳለው የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። ላሊበላ ዓለም አቀፍ የቱሪስት መዳረሻ ከመሆኑ ባለፈ የገና በዓል በድምቀት ስለሚከበርበት በርካታ ቱሪስቶች በተለያዩ የመጓጓዣ አማራጮች ወደ ሥፍራው እንደሚመጡ የቢሮ ኃላፊ መልካሙ ፀጋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል። ቱሪስቱም የተቀናጀ የቱሪዝም አገልግሎትን መሰረት አድርጎ ስለሚመጣ ላሊበላን ብቻ ሳይሆን፤ ሌሎች መዳረሻዎችን አሥተሣሥሮ እንደሚጎበኝም ጠቁመዋል። ይህም እንደ ክልል ያለውን የቱሪዝም ዘርፍ እንዲነቃቃ ያደርገዋል ነው ያሉት ኃላፊው። ክልሉ በባህል፣ በቅርስ፣ በእንግዳ ተቀባይነትና በሌሎች ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ድንቅ ምድር መሆኑን ጠቁመው፤ ሕዝቡ በሚታወቅበት እንግዳ ተቀባይነት ባህሉ ለጎብኚዎች አቀባበል እንዲያደርግም ጠይቀዋል። የክልሉ መንግስትም በዓሉ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር እና ለእንግዶቹም ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የላሊበላ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ መሳይ ወዳጆ በበኩላቸው፤ ከቱሪዝም ጋር የተሣሠረውን የከተማዋን ኢኮኖሚ በይበልጥ በማነቃቃት ረገድ የገና በዓል ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ኢኮኖሚው ከቱሪዝም ጋር መቆራኘቱን የተገነዘበው የከተማዋ ነዋሪም፤ የአካባቢውን ሰላም በማጽናት ለእንግዶች ምቹ አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅቷል ብለዋል።
ሀገር በቀል እውቀቶችን በአንድ ቋት በማሰባሰብ ለሀገር ልማት እንዲውሉ እየተሰራ ነው
Dec 22, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የሚገኙ እምቅ ሀገር በቀል እውቀቶችን በአንድ ማዕከላዊ ቋት በማሰባሰብ ለሀገር ልማትና ለፖሊሲ ግብዓት ለማዋል የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። መንግሥት የሀገር በቀል እውቀቶችን ለሀገራዊ ብልጽግና እና ለማንነት ግንባታ ያላቸውን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ በመገንዘብ፣ እነዚህ እውቀቶች ተጠብቀው እንዲቆዩና ለዘመናዊው የልማት ጉዞ ግብዓት እንዲሆኑ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ በዘመናት ሂደት ያካበተቻቸው በርካታ ሀገር በቀል እውቀቶች ቢኖሯትም፣ እስካሁን በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደራጀ መልኩ ባለመያዛቸው በሚፈለገው መጠን ጥቅም ላይ ሳይውሉ መቆየታቸውም ይገለፃል። ይህንን ክፍተት ለመሙላት የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በየአካባቢያቸው የሚገኙ ጥበቦችን መለየትና መሰነድ በሚችሉባቸው ዘዴዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና እያካሄደ ይገኛል። በስልጠናው መክፈቻ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ እንደገለጹት፣ አሁን የተዘረጋው አሰራር እነዚህን የተበታተኑ እውቀቶች በአንድ ቋት በማሰባሰብ ለትምህርት ስርዓቱ፣ ለምርምርና ለፖሊሲ ግብዓትነት ለማዋል ያስችላል። ይህም ሀገራዊ ችግሮችን በሀገር በቀል መፍትሄዎች ለመፍታት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የኮሚኒቲ ኢንጌጅመንትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ሀላፊ ሰላም አለሙ በበኩላቸው፤ ሀገር በቀል እውቀቶቹን ከመሰነድ ባለፈ በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ እንዲካተቱ የማድረግ ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እምቅ ሀገር በቀል እውቀቶች መኖራቸውን የገለጹት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህብረተሰብ ጤና ትምህርት ክፍል ተመራማሪው ፕሮፌሰር ሚሪጊሳ ካባ ናቸው። እነዚህ ሀገር በቀል እውቀቶችን በመሰነድ ለትምህርት ስርዓት፣ ለፖለሲ አቅጣጫ፣ ለልማትና ሌሎች ስራዎች እንዲውሉ በጋራ እንሰራለን ብለዋል። በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሰቲ የአንኮበር የእጽዋትና ሀገር በቀል እውቀት ልማት ማእከል አስተባባሪ አማረ አያሌው (ዶ/ር) እና በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የሀገር በቀል እውቀት ማእከል አስተባባሪ ያስሚን መሀመድ፤ በየአካባቢው ያሉ ሀገር በቀል እውቀቶችን የማሰባሰብ፣ በቴክኖሎጂ የማስደገፍና በስፋት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም እነዚህን በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደራጀ መልኩ ለማጠናከር ስራዎች መጀመራቸው ውጤታማ ለመሆን ያስችላልም ብለዋል።
ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ተቋማት የሰላም አካቶ ትግበራን የዕቅዳቸው አካል ሊያደርጉ ይገባል
Dec 22, 2025 84
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ተቋማት የሰላም አካቶ ትግበራን በዕቅዳቸውና በሪፖርታቸው አካትተው ሊተገብሩ እንደሚገባ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌደራልና የክልል ምክር ቤቶች በህግ ማውጣት፣ በክትትልና በቁጥጥር ሥራዎቻቸው የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ ሰላም በአንድ ተቋም ብቻ የሚመጣ ሳይሆን በሁሉም ግለሰቦች፣ ተቋማትና አደረጃጀቶች ውስጥ ያለ አንኳር ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሰላም በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ እንዲሁም ከህብረተሰቡ ጋር ባለ መስተጋብር ሁሉ የሚገኝ ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል። ሚኒስትሩ አክለውም፣ ሰላም የሚጀምረው እያንዳንዱ ተቋም ኃላፊነቱን በአግባቡ ከመወጣት መሆኑን ገልጸው፤ የዚህ ድምር ውጤት የሀገርን ሰላም እንደሚያረጋግጥ አስረድተዋል። ከቀበሌ እስከ ፌደራል ያሉ የመንግስት መዋቅሮች አገልግሎት ሲሰጡ የህዝብን ፍላጎትና ተጠቃሚነት መሰረት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸው፣ ተቋማቱ ሰላምና አብሮነትን የሚያጠናክሩ ተግባራትን በዕቅዳቸው ማካተት፣ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቶች ሰላምን ታሳቢ ያደረጉ እንዲሆኑ ማድረግ እና አገልግሎት አሰጣጥን ለሰላም ግንባታ በሚያግዝ መልኩ መቅረፅ እንደሚገባም ተናግረዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋማትን ዕቅድና ክትትል ሲገመግም፣ ስራዎቻቸው ለሀገራዊ ሰላም ከሚያበረክቱት አስተዋፅኦ አንጻር ሊቃኝ እንደሚገባ በመድረኩ የተገለፀ ሲሆን የሰላም የቁጥጥር ስርዓትን ባህል ማድረግም የሰላም አካቶ ትግበራን ስኬታማ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑም ተጠቅሷል። በመድረኩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ምክር ቤቱ ሕዝብን አንድ በሚያደርጉ የሰላምና የልማት ጉዳዮች ላይ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 22, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በፓርላማ ዲፕሎማሲ እና በውክልና ሥራዎች ሕዝብን አንድ በሚያደርጉ የሰላምና የልማት ጉዳዮች ላይ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌደራልና የክልል ምክር ቤቶች የሕግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ሰላም ለሀገር ዕድገት መሠረት መሆኑን አንስተዋል። ይህም ለአርሶ አደሮች ምርታማነት፣ ለነጋዴው ትርፋማነት፣ ለመንግሥት የልማት ውጤታማነትና ለተመራማሪዎች አዳዲስ የፈጠራ ሐሳብ ለማመንጨት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ሰላም በሁላችንም እጅ ያለ እንጂ ከየትም የምናመጣው አይደለም ያሉት ምክትል አፈ ጉባኤዋ፤ የሀገራችንን ሰላም መጠበቅ ከሁሉም ዜጋ የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል። የሰላም ግንባታ የሀገር ግንባታ ሥራ መሆኑን በመግለጽ፤ እየታየ ያለውን ሀገራዊ ሰላም ለማፅናት ሀገራዊ ልማትን ማፋጠን ይገባል ብለዋል። ምክር ቤቱ በፓርላማ ዲፕሎማሲ፣ በውክልና ሥራዎች እና በሌሎችም እንቅስቃሴዎች ሕዝብን አንድ በሚያደርጉ የሰላም ጉዳዮች ላይ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ለዚህ ደግሞ ምክር ቤቱ የተቋማትን የሰላም አካቶ ትግበራ መሠረት በማድረግ ተገቢ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ከዚህም ባለፈ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ሕጎች ሲቀርቡለት ለሰላም ያላቸውን ሚና ታሳቢ በማድረግ መዘጋጀታቸውን ይቆጣጠራል ብለዋል። ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት ለምን ዓላማ አዋሉት የሚለውንም ቁጥጥር እንደሚያደርግ ገልጸዋል። በመድረኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፣ የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
በምዕራብ ሸዋ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 300 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል
Dec 22, 2025 108
አምቦ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦በምዕራብ ሸዋ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 300 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በዞኑ የቶኬ ኩታዬ ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ስራ በዞንና በወረዳ የስራ ኃላፊዎች ተጎብኝቷል። የምዕራብ ሸዋ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲሳ ሀይሉ እንዳሉት፤ በበጋ መስኖ ስንዴ 400 ሺህ ሔክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ ነው ። በእስካሁኑ ሂደትም 320 ሺህ ሄክታር መሬት የማሳ ዝግጅት ተጠናቅቆ 300 ሺህ ሄክታሩ በዘር መሸፈኑን ጠቅሰው አጠቃላይ ከሚለማው መሬትም 12 ነጥብ 6 ኩንታል ምርት ይጠበቃል ብለዋል። የበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱን ስኬታማ ለማድረግ ከባለፉት ዓመታት ተሞክሮ በመውሰድ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ሲደረጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በተለይም የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር በተሻለ መልኩ ማቅረብ እንደተቻለና አርሶ አደሩ የግብርና ፓኬጆችን እንዲተገብርም ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገለት መሆኑን አመልክተዋል። የቶኬ ኩታዬ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ዋዬሳ አለሙ በበኩላቸው፤ በወረዳው የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴን በመተግበር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በወረዳው 20 ሺህ ሔክታር መሬት በስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከ10 ሺህ ሔክታር መሬት በላይ በዘር መሸፈኑን ተናግረዋል። በዛሬው ዕለትም የእቅዱ አካል የሆነው በወረዳው በኢመላ ዳዌ አጆ ቀበሌ 102 ሔክታር መሬት ላይ የስንዴ ዘር የመዝራት መርሃ ግብር መካሄዱን ገልጸው በልማት ስራውም 208 አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም የተሳተፉበት ነው ብለዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የወረዳው አርሶ አደሮች በበኩላቸው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው በዓመት ሶስት ጊዜ ማልማት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። አርሶ አደር አራርሳ ዲልጋሳ እንዳሉት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከጀመሩ ወዲህ የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ አልፈው ገቢያቸው እያደገ ልጆቻቸውን በተሻለ ሁኔታ እያስተማሩ ነው። በዚህ ዓመት ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በኩታ ገጠም በመደራጀት ስንዴ መዝራታቸውን ገልጸው ከአንድ ሄክታር 35 ኩንታል ምርት እንደሚጠብቁም አመላክተዋል። ሌላው የወረዳው አርሶ አደር ገመቹ ደንደና፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በኩታ ገጠም በበጋ መስኖ ስንዴ እያለሙ መሆኑን ገልጸው በዚህም ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዘንድሮም በወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት አማካኝነት የምርት ማሳደጊያ ግብዓት እና ትራክተር ቀርቦላቸው ስራውን በስፋት እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በካፋ ዞን የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው
Dec 22, 2025 57
ቦንጋ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦በካፋ ዞን የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። የቱሪዝም ሚኒስቴር ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማስተዋወቅ ያለመ ጉብኝት በካፋ ዞን ተደርጓል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ እንደገለፁት፤ ዞኑ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶች መገኛ፣ የቱባ ባህልና የበርካታ እሴቶች ባለቤት ከመሆኑም ባለፈ በርካታ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ተከባብረውና ተዋደው የሚኖሩበት የሰላም ተምሳሌት ነው። በዞኑ ፏፏቴዎች፣ ዋሻዎች፣ የካፋ ባዮስፌር፣ ፍልውሃና ሌሎች የጎብኚዎችን ቀልብ የሚይዙ የመስህብ ስፍራዎች መኖራቸውን ገልጸዋል። እንደ ሀገር ለቱሪዝም ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረት መሰረት በማድረግ እነዚህን ሀብቶች በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በአንድ ወረዳ አንድ የለማ የቱሪስት መዳረሻ እንዲኖር በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረትም እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። በቱሪዝም ሚኒስቴር የቱሪዝም ፓኬጅ እና ብራንድ ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ አቶ ማርቆስ ኦልጅራ፣ ኢትዮጵያን ምድረ ቀደምት ሀገር ከሚያስብላት አንዱ የቡና መገኛ መሆኗ ነው ብለዋል። ይህንን ሀብት በደንብ በማስተዋወቅ ወደ ቱሪዝም ሀብትነት ለመቀየር ጥረት እየተደረገ ነው ያሉት ኃላፊው በቡና ልማት የሚታወቀውን የደቡብ የምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢን ለማስተዋወቅ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የማርኬቲንግና ፕሮሞሽን ዳይሬክተር ለምለም አስራት በበኩላቸው፣ በክልሉ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ የዘርፉን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በርካታ ጎብኚዎች አካባቢውን ለመጎብኘት ቢመጡም በቂና ምቹ ማረፊያ ባለመኖሩ የቆይታ ጊዜያቸው አጭር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ደረጃቸውን የጠበቁ ማረፊያዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች የማህበረሰቡን ኑሮ የሚለውጡ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው
Dec 22, 2025 100
ጂንካ ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ኑሮ የሚለውጡ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የመቶ ቀናት ዕቅድ አፈጻጸም የተገመገመበት መድረክ ዛሬ በጂንካ ከተማ ተካሂዷል። የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቆላማ አካባቢ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቲዮስ ጋርሾ እንደገለጹት፤ በክልሉ በመቶ ቀናት ዕቅድ ትኩረት ከተሰጣቸው መስኮች አንዱ በቆላማ አካባቢዎች የማህበረሰቡን ኑሮ የሚለውጡ ተግባራትን ማከናወን ነው። ለዚህም በክልሉ ተረጂነትን ወደ ዜሮ በማውረድ የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የተቀናጀ የመስኖ ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በመስኖ ልማቱ የአርብቶ አደሩ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፣ ይህንን ለማጠናከርም በነዳጅ የሚሰሩ የመስኖ አውታሮችን ወደ ሶላር እና ወደ ኤሌክትሪክ የመቀየር ሥራ ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል። ዘንድሮም በኛንጋቶም ወረዳ የሚገኙ የአይፓ እና ናፑቱኮይት መስኖ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል አማራጭ ለማሸጋገር እንደሚሰራ አስታውቀዋል። በቀጣይም የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጡና የገቢ አማራጭ በመሆን ኑሮን የሚያሻሽሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ ማቲዎስ ተናግረዋል። በተለይ የአርብቶ አደሩ እንስሳት ለድርቅ ያለውን ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያስችሉ የመኖ ልማት ሥራዎች በትኩረት ከሚከናወኑ ተግባራት አንዱና ዋንኛው መሆኑን አስረድተዋል። እንደ አቶ ማቲዮስ ገለጻ፤ በክልሉ በ90 ቀናት ውስጥ ከ90 በላይ ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ተግባራት ለማሰማራት ታቅዷል። በእስካሁንም 25 ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ የገቢ ማስገኛዎች ተደራጅተው በቅርቡ ወደ ሥራ እንደገቡ የገለጹት ኃላፊው፣ ቀሪዎቹን የማደራጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢንተርፕራይዞቹን ውጤታማ ለማድረግም ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር ለማመቻቸት ቢሮው ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ነው ያስታወቁት፡፡
የጎጆ ኢንዱስትሪዎችን በማጠናከር ወደ ትልልቅ ፋብሪካዎች እንዲያድጉ እየተሰራ ነው
Dec 22, 2025 104
ሮቤ ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የጎጆ ኢንዱስትሪዎችን በማጠናከር ወደ ትልልቅ ፋብሪካዎች እንዲያድጉ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ገለጸ። የክልሉ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በሮቤ ከተማ የጎጆ ኢንዱስትሪን ጨምሮ በተለያየ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ወጣቶች የሥራ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል። የኦሮሚያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ኤባ ገርባ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ የወጣቱን የስራ ፈጠራ አቅም የሚያጎለብቱ የጎጆ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ትልልቅ ፋብሪካዎች ለማሳደግ የተለያየ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው። የጎጆ ኢንዱስትሪዎች ሰፊ የስራ እድል መፍጠር የሚችሉ መሆናቸውን ጠቅሰው በዚህ ዘርፍ የተሰማሩ ዜጎች የበለጠ እንዲጠናከሩ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታ እንዲመቻችላቸው እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። እንዲሁም በዘርፉ ወደ ሥራ ለገቡ ወጣቶች አስፈላጊ ማሽኖችን በሊዝ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። ኢንጂነር ኤባ እንዳሉት፤ በክልሉ ባለፉት አምስት ወራት የጎጆ ኢንዱስትሪን ጨምሮ በተለያየ የስራ ዘርፎች የሥራ ዕድል ለተፈጠረላቸው ከ700 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ተመቻችቶላቸዋል። በሮቤ ከተማ በዘርፉ በተሰማሩ ወጣቶች እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት በተሞክሮነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ጠቁመው መንግስት ከዘርፉ ከሚጠብቀው ግብ አንፃር ብዙ መሥራት እንደሚጠይቅ አስረድተዋል። በተለይም የጎጆ ኢንዱስትሪውን ዘርፍ በማጠናከር በርካታ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር ወደ ትልልቅ ፋብሪካዎች እንዲያድጉ ድጋፍና ክትትሉ ይጠናከራል ብለዋል። የሮቤ ከተማ ከንቲባ አቶ ዲኖ አሚን በበኩላቸው፤ በከተማው የወጣቱን የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በከተማዋ ባለፉት አምስት ወራት በተለያዩ ዘርፎች የሥራ ዕድል ለተፈጠረላቸው ከ6 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር መመቻቸቱን በማሳያነት አንስተዋል። በቀጣይም በጎጆ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች ስራቸውን እንዲያስፋፉ የሚያግዙ የግብዓትና የፋይናንስ ድጋፎች እንዲደረግላቸውም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ይሰራል ነው ያሉት። በጎጆ ኢንዱስሪዎች የስራ እድል ከተፈጠረላቸው የከተማዋ ወጣቶች መካከል ደረጄ ወርቅነህ፣ ማህበራቸው ከመንግስት በተመቻቸለት 2 ሚሊዮን ብር ብድር በመኖ ማቀነባበር ዘርፍ ወደ ሥራ በመግባት ውጤታማ መሆኑን ገልጿል። በተሰማሩበት የስራ ዘርፍም ከራሳቸው አልፈው 27 ለሚሆኑ ሌሎች የአካባቢያቸው ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም አንስቷል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች የጥናትና ምርምር ስራዎችን በተቀናጀ አግባብ ሊያከናውኑ ይገባል - የትምህርት ሚኒስቴር
Dec 22, 2025 100
አሶሳ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች የጥናትና ምርምር ስራዎችን በተቀናጀ አግባብ ሊያከናውኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስቴር አስገነዘበ። 3ኛው የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም ዛሬ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። በምክክር መድረኩ የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመማር ማስተማር ሥራቸው በተጓዳኝ የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማከናወን በተለያዩ ዘርፎች ማህበረሰብ ተኮር ለውጥ እንዲያመጡ እየተደረገ ነው። በዚህም ዩኒቨርሲቲዎች የልህቀት ማዕከል ሆነው በሚያከናውኑት የጥናትና ምርምር ስራ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። በተለይም የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች በተቀናጀ አግባብ በየአካባቢው ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘቡ የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማከናወን ተልዕኳቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ጥምረት ሰብሳቢና የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኡባህ አደም(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ፎረሙ ዩኒቨርሲቲዎቹ በጋራ በሚያከናውኗቸው የምርምር ስራዎች ላይ ተሞክሮ ለመቀመርና የተከናወኑ የምርምር ስራዎችን ውጤታማነት ለመገምገም የተዘጋጀ ነው ብለዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበረሰብ ተኮር የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማከናወንና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ተግባራት ላይ እየተሳተፉ መሆናቸውን አንስተዋል። ዩኒቨርሲቲው በተግባር ተኮር መስክ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በግብርና፣ በማዕድንና የተለያዩ ማህበረሰብ ተኮር የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከማል አብዱራሂም(ዶ/ር) ናቸው። በተለይም በማንጎ እና ቀርከሃ ሀብት ላይ እየተከናወኑ የሚገኙ የምርምር ስራዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ በማድረግና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ ላይ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ያሳደጉ ስራዎች መሆናቸውን አንስተዋል። በፎረሙ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ተወካዮች፣ የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ሌሎች የትምህርቱ ዘርፍ አመራሮች ተገኝተዋል። የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም 15 ዩኒቨርሲቲዎችን ያቀፈ ሲሆን አንደኛ ፎረሙን በድሬዳዋ እእንዲሁም ሁለተኛውን በአርሲ ዩኒቨርሲቲዎች ማካሄዱ ይታወሳል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ የሚያስችል አውድ የሚፈጥር ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Dec 22, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የታለመውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ የሚያስችል ምቹ መደላደል እንደሚፈጥር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብሔራዊ የዲጂታል ትራስፎርሜሽን ምክር ቤት ሊቀ መንበር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ለስትራቴጂው ውጤታማነት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ2030 ስትራቴጂን ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብሔራዊ የዲጂታል ትራስፎርሜሽን ምክር ቤት ሊቀ መንበር ተመስገን ጥሩነህ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠናቀቂያ እና በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም ኢትዮጵያ የማደግ ፍላጎት እና የማደግ አቅም ያላት ሀገር ናት ብለዋል። እንደ ሀገር የሚያስፈልገን የማደግ ፍላጎታችንና የማደግ አቅማችንን የሚያገናኝ ስልት ነው ያሉ ሲሆን ይህን የማስተሳሰር አቅም ደግሞ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሆኑ ታምኖበት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። መንግስት የዲጂታል ኢትዮጵያ መርሃ ግብርን የዘረጋው ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሞች፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እና ከአፍሪካ አህጉራዊ የትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂዎች መሆኑን አንስተዋል። በዚሁ መሰረት የተቀረጸው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞ ወደ ሌላ ምዕራፍ ማሸጋገሩን ገልጸዋል። ስትራቴጂው በሀገር ደረጃ የፋይናንስ አሰራርን፣ የአገልግሎት አሰጣጥን፣ የህዝብ ትስስርን፣ የንግድ ስርዓትን፣ የመንግስት ተደራሽነትን፣ የፀጥታ እና ደህንነት አጠባበቅን እንዲሁም የሚዲያ አውድን ጨምሮ የተለያዩ አሰራሮችን መቀየሩን ነው ያመለከቱት። የወጣቶች አስተሳሰብ፣ ስነ ልቦና እና አሰራር ተቀይሯል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተፈጠረው አውድ የዲጂታል ዘርፉ እንዲያድግ ቁልፍ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ኢትዮጵያ ወደ አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ የተሸጋገረችበት መሆኑን ገልጸው ስትራቴጂው በቅርቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መፅደቁን አስታውሰዋል። አዲሱ ስትራቴጂ በጋራ ጥረት፣ ትጋት እና ትብብር የተጀመሩ የዲጂታል ውጥኖች በፍጥነት የሚስፋፉበት፣ ተናባቢ የዲጂታል ስነ-ምህዳር የሚገነባበት፣ ዘላቂ የዲጂታል እምርታ የሚመጣበትና ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የሚረጋገጥበት ማዕቀፍ ነው ብለዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዜጎችን ማዕከል ያደረገ መንግስታዊ ስርዓት የበለጠ የሚሰፋበት፣ ሁሉን አቀፍ አካታች የዲጂታል አገልግሎቶች የሚቀርቡበት፣ ሉዓላዊ እና ደህንነታቸው የተጠበቀ የዲጂታል ስርዓቶች የሚበራከቱበት እንዲሁም የውስጥ ፈጠራ የሚበረታታበት አንደሆነም አስገንዝበዋል። ይህም አጠቃላይ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገትና ትራንስፎርሜሽን በማረጋገጥ ወደ ምንመኘው ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚፋጠንበት አውድ ይሆናል ሲሉ ገልጸዋል። መንግስት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እንዲተገበር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ እና ሁሉም ባለድርሻ አካል ለስኬታማነቱ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
ታለንት ወሳኝ መሰረተ ልማት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Dec 22, 2025 109
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 13/2018(ኢዜአ)፡- ታለንት ወሳኝ መሰረተ ልማት በመሆኑ ከሌሎች ልማቶች እኩል ኢንቨስት ማድረግ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠቃለያ እና በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በይፋ የማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ከተሳታፊዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራርያ፤ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች ተወዳዳሪዎቻቸውን የሚበልጡበት አንዱ አቅም ተሽሎ መገኘት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መንግስት በጤና እና በሌሎች ዘርፎች የሚሰሩ ፈጠራዎችን እንደሚያበራታታ እንዲሁም አግዞ እንደሚጠቀምም አረጋግጠዋል፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ዋነኛ ዓላማ ቢያንስ ሀገር በቀል ሮቦት፤ ስልክ እና አይፓድ መፍጠር የሚያስችል የሀርድዌር ማምረቻ የመገንባት አቅም መፍጠር መሆኑን ገልጸው ይህም ከሶፍትዌር ወጥተን ሀርድዌር የመገንባት እድል ይፈጥርልናል ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል የቡና ኤክስፖርት በ3 እጥፍ ማደጉን በመግለጽ ይህንን በዲጂታል ማገዝና እሴት ጨምሮ መላክ እንደሚገባ እና ለዚህም መንግስት አበክሮ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ መንግስት ከኢትዮጵያ ገበያ አልፈው ወደ አፍሪካ ገበያ ምርቶቻቸውን የሚወስዱ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን በሙሉ አቅሙ እንደሚደግፍም ተናግረዋል፡፡ መንግስት እንደ ኤሌክትሪክ፤ መንገድና ቴሌኮሙኒኬሽን ሁሉ ታለንት ወሳኝ መሰረተ ልማት ነው ብሎ ያምናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህም በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን አብራርተዋል፡፡ በኢንሳ የተጀመረውና ተጠናክሮ የቀጠለው የሰመር ካምፕ፣ በአብርሆት ቤተመጽሀፍት በየዓመቱ የሚሰናዳው የሮቦት ውድድር እና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በቅርቡ ያስጀመረው የስታርታፕ መሰረተ ልማት የተሟላለት ህንጻ ለዚህ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ጥራት ያላቸው የመንግስት መስርያ ቤቶች እና ለስታርታፕ ተብለው የተዘጋጁ ቦታዎች መፈጠራቸውንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ከምንሰራው ስራ እኩል ታለንት ላይ ኢንቨስት ልናደርግ ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ትናንሽ ስታርታፖች እንዲያድጉና እንዳይጠፉ ማድረግ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ድርብ ኃላፊነት መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው አስገንዝበዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትልሞች በሦስት ዋና ጉዳዮች ያተኩራሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Dec 22, 2025 121
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 12/2018(ኢዜአ)፡- የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትልሞች በዋናነት በሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠቃለያ እና በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ የማስመጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዋና ራዕዩን ሰብሰብ አድርገን ስንገልጸው ሦስት ነገሮችን ለማሟላት ያለመ ነው ብለዋል። በዚህም መሠረት የመጀመሪያው አቅርቦት(አክሰስ) መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ሁሉም ዜጎች ካሉበት ሆነው የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉበትን ዕድል መፍጠር መሆኑን አስረድተዋል። በመሆኑም ዜጎች እኩል እድል እና እኩል አገልግሎት እንዲያገኙ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የመጀመሪያ ትልሙ አቅርቦት ነው ብለዋል። ሁለተኛው ዕድል(ኦፖርቹኒቲ) መሆኑን አመላክተው፤ እኩል እድል ባልሰጠንበት መስክና ሁኔታ እኩል ተጠቃሚ መሆን አይቻልም ነው ያሉት በማብራሪያቸው። በጾታ፣ በአካል ጉዳት ወይም በርቀት ምክንያት ዜጎች ሊያገኙ የሚገባውን እድል እኩል የሚያመቻች ሥርዓት መፍጠር እንደሚያስፈልግም ነው ያስገነዘቡት። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲያሳካ ከሚፈለጉት ጉዳዮች አንዱ ለዜጎች እኩል እድል መስጠት መሆኑንም አመላክተዋል። ሦስተኛው ዲጂታል ኢትይጵያ 2030 እንዲያሳከው የሚፈለገው ትልም መተማመን(ትረስት) መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም መሠረት በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመን ካልተፈጠረ፤ የገንዘብ ዝውውር፣ መማር ማስተማር፣ ለጤና ዳታ መስጠት፣ ደፍሮ ለሥራ ማመልከት፣ የግል መረጃን በክላውድ ላይ ማስቀመጥ የሚታሰብ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል። ቴክኖሎጂ አሳላጭ መሆን ተስኖት በጥርጣሬ የሚታይና የሚፈራ ብሎም ዜጎች የማያምኑበት ከሆነ የምናስበውን ነገር አያሳካም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በገለጻቸው። ሦስቱ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትልሞች አቅርቦት፣ ዕድል እና መተማመን ተደምረው ለዜጎች በርከት ያለ የሥራ ዕድል መፍጠር ብሎም ለሀገር ዕድገት ማረጋገጥ አለባቸው ብለዋል። ሥራ እና ዕድገት ብቻውን በቂ እንዳልሆነ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ ሉዓላዊነትንም የሚያረጋግጥ መሆን እንዳለበት አስረድተዋል። ስለዚህ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ከላይ በተገለጹት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የኢትዮጵያን ብልጽግና ከሚያረጋግጡ ዋና ዋና ሴክተሮች(ምሠሦዎች) አንዱ ሆኖ ያገለግላል ተብሎ በመንግሥት መታሰቡን አውስተዋል። በመሆኑም በትብብር ከሠራን ይህን ራዕይ እንደምናሳካ ሙሉ እምነት አለኝ ሲሉም ተናግረዋል። #DigitalEthiopia2030
ስፖርት
በአፍሪካ ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ አንጎላን አሸነፈች
Dec 22, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት የመጀመሪያ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ አንጎላን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ማምሻውን በማራካሽ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኦስዊን አፖሊስ እና ላይል ፎስተር የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ማኑኤል ሉዊስ ዳ ሲልቫ ካፉማና (በቅጽል ስሙ ሾው) ለአንጎላ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጨዋታው ተመጣጣኝ እና አዝናኝ ፉክክር ተደርጎበታል። ውጤቱን ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ ምድብ ሁለትን በሶስት ነጥብ መምራት ጀምራለች። በዚሁ ምድብ ምሽት አምስት ላይ ግብጽ ከዚምባቡዌ በአጋዲር ስታዲየም ይጫወታሉ።
ማሊ እና ዛምቢያ አቻ ተለያዩ
Dec 22, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ ሁለተኛ ጨዋታ ማሊ እና ዛምቢያ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በመሐመድ አምስተኛ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ላሲን ሲናዮኮ በ61ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ማሊን መሪ ሆና ነበር። ይሁንና ፓትሰን ዳካ በ92ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ግብ ለዛምቢያ ወሳኝ አንድ ነጥብ አስገኝታለች። ማሊ በ41ኛው ደቂቃ ያገኘችውን ፍጹም ቅጣት ምት ኤል ቢላል ቱሬ አምክኖታል። ውጤቱን ተከትሎ ማሊ እና ዛምቢያ በውድድሩ የመጀመሪያ ነጥባቸውን አግኝተዋል። በምድብ አንድ ትናንት አዘጋጇ ሞሮኮ ኮሞሮስን 2 ለ 0 በማሸነፍ በሶስት ነጥብ ምድቡን እየመራች ነው።
የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎች የሚካሄዱባቸው የሞሮኮ ስታዲየሞች
Dec 22, 2025 109
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት መካሄድ ከጀመረ ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። ጨዋታዎቹ በስድስት ከተሞች የሚገኙ ዘጠኝ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎች የሚደረጉባቸውን ስታዲየሞች መረጃ ከዚህ እንደሚከተለው ይዘን ቀርበናል። 1. ፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም በራባት ከተማ የሚገኘው ስታዲየም 69 ሺህ 500 ተመልካቾችን የሚያስተናገድ ሲሆን በሚይዘው የተመልካች ብዛት ከቀዳሚዎቹ መካከል የሚጠቀስ ነው። ስታዲየሙ የውድድሩን የመክፈቻ ጨዋታ ትናንት አስተናግዷል። የፍጻሜ ጨዋታውን ጨምሮ ቁልፍ የምድብ ጨዋታዎች እና አንድ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ይደረግበታል። ፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ከእ.አ.አ 2023-25 ባለው ጊዜ የካፍ እና ፊፋ መመዘኛዎችን እንዲያሟላ በድጋሚ ተገንብቷል። ለመልሶ ግንባታው 75 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚሆን ገንዘብ ወጪ ተደርጎበታል። 2. የታንጂየር ግራንድ ስታዲየም በታንጂየር ከተማ የሚገኘው ስታዲየም 75 ሺህ 600 ተመልካች ያስተናግዳል። ይህም የአፍሪካ ዋንጫን ከሚያስተናግዱ ስታዲየሞች ከፍተኛ ተመልካች የሚይዘው ሜዳ ያደርገዋል። ስታዲየሙ በ360 ሚሊየን ዶላር ገደማ በሆነ ወጪ እኤአ ከ2023 እስከ 2025 እድሳት የተደረገለት ተደርጎለታል። በአፍሪካ ዋንጫው የጥሎ ማለፍ፣ የሩብ ፍጻሜ እና የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። 3. የንጉስ መሐመድ አምስተኛ ስታዲየም በወቅቱ የሞሮኮ ንጉስ መሐመድ አምስተኛ የተሰየመው ስታዲየም እ.አ.አ በ1955 የተከፈተ አንጋፋ ስታዲየም ሲሆን ለአፍሪካ ዋንጫው እድሳት ተደርጎለታል። ስታዲየሙ 45 ሺህ ተመልካች ያስተናግዳል። ስታዲየሙ በርካታ የሞሮኮ ተቀናቃኝ ክለቦች የደርቢ ጨዋታዎችን አስተናግዷል። የምድብ ጨዋታዎች፣ የጥሎ ማለፍ እና የደረጃ ጨዋታዎች ይደረጉበታል። 4. የማራካሽ ስታዲየም በታሪካዊቷ ማራካሽ ከተማ የሚገኘው ይህ ስታዲየም 45 ሺህ 240 ተመልካቾችን ያስተናግዳል። እ.አ.አ በ2025 በተጠናቀቀው የስታዲየሙ የመጀመሪያ ምዕራፍ እድሳት ሞሮኮን 84 ሚሊዮን ዶላር ገደማ አስወጥቷታል። ስታዲየሙ የምድብ፣ የጥሎ ማለፍ እና የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ይደረጉበታል። 5. የአጋዲር ስታዲየም በደቡብ አትላንቲክ ጠረፍ እና በአትላስ ተራሮች አቅራቢያ የሚገኘው ስታዲየም 45 ሺህ 480 ተመልካቾችን ያስተናግዳል። የስታዲየሙ ንድፍ (ዲዛይን) የአትላስ ተራሮችን አምሳያ በያዘ መልኩ የተሰራ ነው። አጋዲር ስታዲየም የምድብ እና የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ይደረጉበታል። 6. የፌዝ ስታዲየም ስታዲየሙ በሰሜን ምስራቅ ሞሮኮ በምትገኘው እና በተለምዶው የሞሮኮ የባህል መዲና እየተባለች በምትጠራው ፌዝ ከተማ የሚገኝ ነው። 45 ሺህ ተመልካች ገደማ የሚያስተናግደው ይህ ስታዲየም ከውድድሩ በፊት ለተደረገላት እድሳት ከ65 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ተደርጎበታል። ስታዲየሙ የምድብ እና የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ይካሄዱበታል። 7. ሙላይ ኤል ሀሰን ስታዲየም የአፍሪካ ዋንጫ በራባት ከተማ እንዲያስተናግዱ ከተዘጋጁት አራት ስታዲየሞች አንዱ ነው። 22 ሺህ ገደማ ተመልካቾች የሚያስተናግደው ስታዲየም ለአፍሪካ ዋንጫ መልሶ ግንባታ ተደርጎለታል። ስታዲየሙ የምድብ እና የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ይካሄዱበተራል። 8. ራባት ኦሊምፒክ ስታዲየም ግንባታው ዘጠኝ ወር ብቻ የፈጀው ይህ ስታዲየም የተጠናቀቀው እ.አ.አ በ2025 ነው። የካፍ መመዘኛዎችን ያሟላው ስታዲየም 21 ሺህ ተመልካች ያስተናግዳል። ለእድሳቱ 50 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ ወጥቶበታል። ስታዲሙ የምድብ ጨዋታዎችን ብቻ ያስተናግዳል። 9. አል መዲና ስታዲየም በቀድሞ አጠራሩ አል ባሪድ ስታዲየም ይባል የነበረው የአሁኑ አል መዲና ስታዲየም በራባት ከተማ የሚገኝ ሲሆን 18 ሺህ ገደማ ተመልካቾችን ይይዛል። የስታዲየሙ ግንባታ 65 ሚሊዮን ዶላር ፈጅቷል። በቅርቡ የተገነባው ስታዲየሙ ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ያሟሉ ዘመናዊ መሰረተ ልማቶች ተሟልተውለታል። በራባት ከተማ የሚገኘው ስታዲየም የምድብ ጨዋታዎች ይደረጉበታል። የሞሮኮ መንግስት ለስታዲየሞች እድሳት እና ግንባታ ከ500 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ እንዳደረገ ይፋዊ የመንግስት መረጃዎች ያመለክታሉ። ስታዲየሞቹ ከ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ባለፈ ሞሮኮ እ.አ.አ በ2030 ከፖርቹጋል እና ስፔን ጋር በጣምራ ለምታዘጋጀው 24ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫም ያገለግላሉ።
በአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
Dec 22, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። በምድብ አንድ ማሊ ከዛምቢያ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ በመሐመድ አምስተኛ ስታዲየም ይጫወታሉ። ማሊ በአፍሪካ ዋንጫ ስትሳተፍ የአሁኑ ለ14ኛ ጊዜ ሲሆን ዛምቢያ 19ኛ ተሳትፎዋን ታደርጋለች። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። እ.አ.አ በ1994 በቱኒዚያ በተካሄደው 19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተገናኝተው ዛምቢያ 4 ለ 0 አሸንፋለች። ማሊ የአፍሪካ ዋንጫን አሸንፋ አታውቅም። ዛምቢያ አንድ ጊዜ የዋንጫ ባለቤት ሆናለች። በዚሁ ምድብ ትናንት በተደረገ ጨዋታ አዘጋጇ ሞሮኮ ኮሞሮስን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በምድብ ሁለት ደቡብ አፍሪካ ከአንጎላ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በማራካሽ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ዋንጫ ሲገናኙ የአሁኑ ለስድስተኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው አምስት የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ደቡብ አፍሪካ ሁለት ጊዜ ስታሸንፍ በቀሪ ሶስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። አንጎላ በአህጉራዊው መድረክ ደቡብ አፍሪካን ለመጀመሪያ ጊዜ ለማሸነፍ ትጫወታለች። የአንድ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ደቡብ አፍሪካ 12 ተሳትፎዋን ታደርጋለች። በአፍሪካ ዋንጫው ለ10ኛ ጊዜ የምትሳተፈው አንጎላ ወደ ጥሎ ማለፍ ከመግባት የዘለለ ታሪክ የላትም። በምድብ ሁለት ሌላኛው መርሃ ግብር ግብጽ ከዚምባቡዌ ምሽት አምስት ላይ በአጋዲር ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሀገራቱ በአፍሪካ ዋንጫው ላይ ሲገናኙ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ነው። ከዚህ በፊት የነበሩትን ሁለት ጨዋታዎች ግብጽ አሸንፋለች። ግብጽ የአፍሪካ ዋንጫን ሰባት ጊዜ በማንሳት ስኬታማዋ ሀገር ናት። የዘንድሮውን ጨምሮ በአፍሪካ ዋንጫ ለ27ኛ ጊዜ በመሳተፍ የተሳትፎ ክብረ ወሰን ባለቤት ነው። ተጋጣሚዋ ዚምባቡዌ ለስድስተኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ታደርጋለች። ብሄራዊ ቡድኑ በተሳትፎዎቹ ላይ ከምድቡ አልፎ አያውቅም ። ጨዋታዎቹ ተመጣጣኝ ፉክክር ይደረግባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
አካባቢ ጥበቃ
በሚቀጥሉት አስር ቀናት በተወሰኑ የመኸር ሰብል አብቃይ አካባቢዎች አልፎ አልፎ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ሊከሰት ይችላል
Dec 22, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት በተወሰኑ የመኸር ሰብል አብቃይ አካባቢዎች አልፎ አልፎ ሊከሰት ከሚችል ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታዎች የተሻለ ገጽታ እንደሚኖረው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ። በአብዛኛዎቹ የመኸር ሰብል አብቃይ በሆኑ የሰብል ስብሰባና ድህረ ሰብል ስብሰባ ተግባራት እየተከናወነ በሚገኝባቸው አካባቢዎች ላይ ደረቃማ እርጥበት ሁኔታ እንደሚጠበቅ ገልጿል። በሚቀጥሉት አስር ቀናትም በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ መካከለኛና ሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሰብል ላይ ጉዳይ ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝቧል። ህብረተሰቡም ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሰብል ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፏል። በዚህም በደረቅ ቀናት የደረሱ ሰብሎችን መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ጠቁሟል። በተቀሩት የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተስተዋለው ደረቃማ የአየር ሁኔታም የደረሰ ሰብል ለመሰብሰብና ለድኅረ ሰብል ስብሰባ ሥራ አመቺ የአየር ሁኔታ መፍጠሩን አስታውቋል። ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ኢትዮጵያ የሚነፍሰው ደረቅና ቀዝቃዛ የአየር ጠባይ እንደሚቀጥልም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የበጋው ደረቅ፣ ጸሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚስተዋል ሲሆን የሌሊትና የማለዳው ቅዝቃዜ እንደሚስተዋልም አስገንዝቧል። በዚህም በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መካከለኛውና ደቡብ ደጋማ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል። ባለፉት ቀናት በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ከነበረው የደመና ሽፋን መጨመር ጋር ተያይዞ በደጋማ አካባቢዎች ላይ የነበረው ቅዝቃዜ እንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደነበረው ገልጿል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት ከመገንባት ባለፈ ለብዝሃ ሕይወት መጠበቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው
Dec 20, 2025 156
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እያከናወነች ያለው ተግባር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት ከመገንባት ባለፈ ለብዝሃ ሕይወት መጠበቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ገለጸ። በኢትዮጵያ በየዓመቱ በስፋት የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነትና መሪነት የተጀመረ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ለመመከት፣ የአገሪቷን የደን ሽፋን ለማሳደግና በአረንጓዴ ልማት ላይ የተመሰረተ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያለመ ሲሆን፤ ባለፉት ዓመታት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሳተፍ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ በማድረግ ረገድ ዓለም አቀፍ እውቅናን ያተረፈ ስኬታማ ተግባር ተመዝግቧል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ካርታ ካስኬ (ዶ/ር) እንዳሉት ፤ የአየር ንብረት ለውጥ በብዝሃ ሕይወት ህልውና ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ በማሳደር ለሥነ-ምህዳር መመሰቃቀልና ለዝርያዎች መጥፋት ዋነኛ መንስኤ እየሆነ ይገኛል። ይህንን ስጋት ለመቀነስና የአየር ንብረት ለውጥን ለመመከት የሚከናወኑ ተግባራት ከፍተኛ ለውጥ እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እያከናወነች ያለው የችግኝ ተከላ ተግባር፣ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት እውን ለማድረግ መሠረት እየጣለ መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የገለጹት። እንደ ካርታ ካስኬ (ዶ/ር) ማብራሪያ፣ የምግብ ሥርዓት ከግብርና ምርታማነትና ከብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ፣ ኢንስቲትዩቱ ይህንን ሥርዓት ለማጠናከር የተለያዩ የአሰራር ስልቶችን ዘርግቶ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል። ለአብነትም የማህበራዊ ዘር ባንኮች ጥምረት አንዱ ሲሆን፤ ይህም በየአካባቢው ያሉና የማይበገር የምግብ ሥርዓትን እውን ማድረግ የሚያስችሉ የሰብል ዝርያዎችን መጠበቅ ያስችላል ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለአካባቢ ጥበቃና ደህንነት መረጋገጥ ትልቅ ማሳያ ተደርጎ እንደሚወሰድ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ይህም የብዝሃ ሕይወት ሀብትን በአግባቡ ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እያገዘው መሆኑን ገልጸዋል።
በጊምቢ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ንጹህ አካባቢን ፈጥሯል
Dec 19, 2025 160
ጊምቢ፤ ታህሳስ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በጊምቢ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተማዋን የቆሻሻ አወጋገድ ክፍተቶች በማረም ንጹህ አካባቢ እንዲኖረን አድርጓል ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነዋሪዎች፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ውብ እንድትሆን ከማድረግ ባለፈ የነዋሪዎችን የአኗኗር ዘይቤ እየቀየረ ስለመምጣቱም አክለዋል፡፡ የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት አቶ ኢዶሳ ገቢሳ፤ የኮሪደር ልማቱ በአካባቢያቸው ያለውን ሀብት እንዲገነዘቡ ከማድረግ ባለፈ ንጹህና ለኑሮ ምቹ አካባቢ መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በኮሪደር ልማት ስራው ልዩ የእግረኛ መንገድ፣ ንጹህ አረንጓዴ ስፍራና ውበትን የሚጨምሩ የመንገድ መብራቶች ዝርጋታ በመከናወኑ ለነዋሪዎች በእግር ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋ ውበትን እንድትጎናጸፍ እና በአኗኗር ዘይቤያችን ላይ ለውጥ እንዲመጣ አድርጓል ያሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ ላሊሳ ቡልቲ ናቸው። በተጨማሪም የልማት ስራው ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ የቆሻሻ አወጋገድ ክፍተቶችን በመቅረፍ ንጽህናው የተጠበቀ፣ ተስማሚና ውብ አካባቢ እንዲኖረን አስቸሏል ብለዋል፡፡ ሸህ ሁሴን ጌታሁን የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው፤የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገጽታ በአጭር ጊዜ ውስጥ በመቀየር ውበትን እንድትጎናጸፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ የጊምቢ ከተማ አስተዳዳር ከንቲባ አቶ ፈዬራ አቦማ፤በከተማዋ የኮሪደር ልማት ሥራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው ቀሪ ስራውን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የኮሪደር ልማቱ የእግረኛና የተሽከርካሪ መንገዶች እንዲሁም አረንጓዴ ስፍራዎችን አካቶ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው እስካሁን ወደ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚጠጋ የኮሪደር ልማት ስራ መከናወኑን አብራርተዋል። በተለይም የኮሪደር ልማት ለዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩ በላይ ከዩኒቨርሲቲዎች ለተመረቁ ወጣቶች በትምህርት ቆይታቸው የቀሰሙትን በተገቢው በመተገበር ገቢ እንዲያገኙ እያስቻለ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ የጊምቢ ከተማን ለኑሮ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ከንቲባው አረጋግጠዋል፡፡
በዞኑ ከ251 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ይከናወናል
Dec 19, 2025 134
ጊምቢ፤ ታህሳስ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ወለጋ ዞን ከ251 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እንደሚከናወን ተገለጸ፡፡ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ከ33 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ማልማት መቻሉን ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል። ዘንድሮም ይኸው ተግባር በተለያዩ ክልሎች በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን በኦሮሚያ ክልልም የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው አርሶ አደሮችን ባሳተፈ መልኩ እየተካሄደ ነው። በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ከ3 ሚሊዮን ሄክታር በላይ የሚሆን መሬትን ወደ ልማት እንዲገባ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የማጎልበት ስራ ተሰርቷል። አሁን ላይም በክልሉ በሚገኙ ዞኖች የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን ከነዚሁ ዞኖች አንዱ በሆነው በምዕራብ ወለጋ ዞን በተያዘው የበጋ ወራት ከ251 ሺህ ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እንደሚከናወን የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት አስታውቋል። በጽህፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ እንደተናገሩት፤ በዞኑ በለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የአፈር መሽርሸርን በማስቀረት፣ የከርስ ምድርና ገጸ ምድር ውሀ ሀብት በመጨምርና የግብርና ምርታማነት በማሳደግ በኩል ተጨባጭ ለውጥ አምጥተዋል፡፡ በዘንድሮ በጋ ወራትም በ251 ሺህ 471 ሄክታር መሬት በላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸው በስራውም ከ400 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ አክለዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ በንቃት እንዲሳተፉ በማድረግ የእርከን ስራዎች፣ የውሃ መቀልበሻ ቦዮችና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል፡፡ ስራውን ለማሳካትም ካለፉት ዓመታት የተገኙ ልምዶችን በመቀመር የህብረተሰብ ንቅናቄ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል። ባለፉት ጊዜያት በተከናወኑት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ከልማት ወጪ የነበሩ አካባቢዎች ዳግም ወደ ልማት መግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአካባቢዎቹ መልማትም ህብረተሰቡ አካባቢውን እየጠበቀ ከልማቱ ጋር የተሳሰሩ እንደ የንብ ማነብ፣ የከብቶች መኖ ልማት እና ሌሎች የልማት ተግባራትን እንዲያከናውን ዕድል እንደተፈጠረለት ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 149
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት ምን አሉ?
Dec 17, 2025 346
የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በአድዋ ድል መታሰቢያም የአበባ ጉንጉን አኑረዋል። ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት በስፋት ዘግበውታል። ዓለም አቀፍ የዜና ወኪሎቹ ሮይተርስ እና አሶሲዬትድ ፕሬስ ጉብኝቱን ከ"ጂኦ-ፖለቲካዊ" አንጻር ተመልክተውታል። በተለይ ህንድ በኢትዮጵያ ያላትን የአምስት ቢሊዮን ኢንቨስትመንት አጉልተዋል። አልጀዚራ ትኩረቱን ያደረገው ህንድ በ"ደቡባዊው ዓለም" (Global South) ላይ ያላትን ተጽዕኖ ለማሳደግ በምታደርገው ጥረት ላይ ነው። እንዲሁም የኢትዮጵያና የህንድ ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመካከለኛው ምስራቅና በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ፋይዳም በስፋት አንስቷል። ቢቢሲ እና ፍራንስ 24 ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለየት ያለ አቀባበል ትልቅ የዲፕሎማሲያዊ መቀራረብ ምልክት መሆኑን ዘግበውታል። የአፍሪካ ሚዲያዎች በበኩላቸው የናሬንድራ ሞዲን ጉብኝት "የአፍሪካ-ህንድ" ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ አድርገው ዘግበዋል። አፍሪካ ኒውስ እና ዘ ኢስት አፍሪካን ጉብኝቱ በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መደረጉን በማንሳት፣ ህንድ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ወታደራዊ፣ የጤና እና የቴክኖሎጂ ትብብር እንደሚያጠናክረውም ገልጸዋል። የደቡብ አፍሪካው ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ የናይጄሪያ እና ሌሎች የአፍሪካ መገናኛ ብዙሃን ህንድ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ኢትዮጵያን እንደ መግቢያ በር (Anchor) መጠቀሟን እና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የሚኖረውን ተምሳሌትነት ዘግበዋል። እንደ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ (The Times of India) ፣ ኤንዲቲቪ (NDTV) እና ኤኤንአይ (ANI) ያሉ የህንድ መገናኛ ብዙሃን የሞዲን ጉብኝት ከፍተኛ ሽፋን ሰጥተውታል። የዘገባዎቹ ዋንኛ ትኩረት በኢትዮጵያ ፓርላማ ስላደረጉት ንግግር እና ስለተደረገላቸው ልዩ የክብር ሽልማት ነው። በሌላ በኩልም የዲጂታልና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተደረጉ ስምምነቶችን በዝርዝር አቅርበዋል። አጠቃላይ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ትኩረት ታሪክ፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነት፣ የደቡብ ለደቡብ ትብብር ላይ ያጠነጠኑ ናቸው። የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ መሸጋገሩንም በመገናኛ ብዙሃኑ በስፋት ተነስቷል። ኢትዮጵያ እና ህንድ የተባበሩት መንግስታ ድርጅት እና ብሪክስን ጨምሮ በሌሎች የባለብዙወገን መድረኮች ላይ የደቡባዊውን ዓለም ድምፅ ለማሰማት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸው በዘገባዎቹ በስፋት ተንጸባርቋል።
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 749
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል። በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 641
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 77
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 487
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 814
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል። የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 1012
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 615
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3074
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 3011
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3911
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2485
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1594
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7411
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5898
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር ተሻጋሪ ወዳጅነት
Dec 16, 2025 369
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 904
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው። እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም። የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል። የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል። ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!