ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና በማጎልበት ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል
Jul 7, 2026 23
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና በማጎልበት ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) አባል አገራት የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ላይ ያተኮረ የሁለት ቀናት አውደ ጥናት እየተካሄደ ይገኛል። በአውደ ጥናቱ መክፈቻ ላይ በግብርና ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ ዜና ሀብተወልድ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ለማስፋፋት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል። የመስኖ ስንዴ ልማት፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የአፈር መሸርሸርን መከላከልና ጤንነትን የመጠበቅ፣ የእንስሳት ምርታማነትን የማሻሻያና ሌሎች ስራዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ለማጎልበት የተገኙ ውጤቶች ለኢጋድ አባል ሀገራት ተሞክሮ የሚውሉ መሆናቸውን አመልክተው፤ በቀጣናው የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል የግብርና ልህቀት ማዕከል ለማቋቋም ግብዓት እንደሚሆን አንስተዋል። የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም ስራዎች በአንድ ሀገር ብቻ የሚከናወን ሳይሆን የአገራት ቅንጅት የሚያስፈልግ በመሆኑ ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ጋር የሚከናወኑ ተግባራትን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢጋድ አባል ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ከመቋቋም አኳያ ያሉበት ደረጃ ላይ ያተኮረ ጥናት መካሄዱን ገልጸዋል። በአውደ ጥናቱ ውይይት የሚቀርበው ጥናት የአባል አገራትን የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የልህቀት ማዕከላትን ለማቋቋም፣ ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን የመቋቋም አቅምን ለመገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል። በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) የግብርና እና አካባቢ ጥበቃ ዳይሬክተር ዳሄር ኤልሚ በመወከል የኢጋድ የፖሊሲና የምግብ ዋስትና ኤክስፐርት ሲልቪያ ሄንጋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአየር ንብረት ለውጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አምራች አርሶ አደሮችን እየጎዳ ይገኛል ። የሙቀት መጠን መጨመር፣ ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋዎች፣ የመሬት መራቆት፣ የምግብ ዋስትናና ሌሎች ችግሮች የኢኮኖሚ እድገትን እና ዘላቂ ልማትን እያደናቀፉ ይገኛሉ ብለዋል። በመሆኑም፣ የመቋቋም አቅም ያለው ግብርና፣ ምርታማ እና ዘላቂ የምግብ ሥርዓትን ለመገንባት የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ወሳኝ መሆኑን ነው የገለጹት። በሳይንስ፣ በማስረጃ እና ውጤታማ በሆኑ የእውቀት ሽግግር ላይ የተመሰረቱ ፈጠራ የታከለባቸው እና የተቀናጁ ቀጣናዊ ምላሾችን ይሻሉ ብለዋል። አውደ ጥናቱ የኢጋድ አባል አገራት የምግብ ሥርዓቶች የመቋቋም አቅም ፕሮግራም ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው፤ የቀጣናውን ተጨባጭ ሁኔታዎች በትክክል የሚያንፀባርቅ እና ወደ ተግባር ሊቀየሩ የሚችሉ ምክረ-ሃሳቦች እንዲሁም ቴክኒካዊ እውቀት ለማጎልበት ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው
Jul 7, 2026 28
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ገለጹ። የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) የቀጣናውን የኃይል ንግድ በይፋ ለማስጀመር የሚያስችልና አባል ሀገራትን መግባባት ላይ የሚያደርስ ልዩ ስብሰባ ማካሄድ ጀምሯል። ይህ መድረክ አባል ሀገራትን መግባባት ላይ ለማድረስና የቀጣናውን የኃይል ንግድ በይፋ ለመክፈት ያለመ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣናው አስተማማኝና ዘላቂ አቅርቦት ለመፍጠር የምታደርገውን ጥረት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። ይህ የኃይል ትስስር ለኢትዮጵያ ትልቅ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ባለፈ፣ በአባል ሀገራቱ መካከል በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ዘርፎች ጠንካራ መስተጋብር እንዲፈጠር እያደረገ ይገኛል ብለዋል። በአሁን ወቅት ይህንን ቀጣናዊ መስተጋብር ወደ አንድ የጋራ የአፍሪካ የኃይል ትስስር ለማሳደግ መጠነ-ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) ሊቀመንበር ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፤ የኃይል ትስስሩ ለሀገር በርካታ ጥቅሞች እንዳሉት አብራርተዋል። የኢትዮጵያን ቀጣናዊ ተሰሚነትና የዲፕሎማሲ አቅም ከማሳደግ ባለፈ፤ ከኃይል ሽያጭ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ እያስቻላት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት ከኬንያ፣ ሱዳን፣ ጂቡቲና ታንዛኒያ ጋር ስምምነት በመፍጠር ኃይል እያቀረበች መሆኗን ጠቁመዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም፤ በቀጣይም ከደቡብ ሱዳን እና ከሶማሊያ ጋር የኃይል ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል
Jul 7, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነት ማሳደጉን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው፣ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም፤ መንግሥት የጀመራቸው አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ተከታታይ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ማስቻሉን ገልጸዋል። ግብርና 7 ነጥብ 7 በመቶ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዘንድሮ 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ኩንታል ምርት ተሰብስቧል ብለዋል። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማስፋፋትና ለማዘመን ከተያዙ ቁልፍ ዘርፎች መካከል የኢንዱስትሪው ክፍለ-ኢኮኖሚ ዋነኛውና የትኩረት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል። ከለውጡ በፊት በሀገሪቱ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ በታች የነበረው የማምረት አቅም አሁን ላይ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እፀገነት መንግስቱ እንዳሉት፤ በአምስት ዓመታት የምክር ቤት ዘመን ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እመርታን አስመዝግባለች። በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመትም በብዝኅ ኢኮኖሚ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የተኪ ምርት አቅምን በማሳደግ በወጪ ንግድ ጭምር ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአመራር ቁርጠኝነት፣ የዜጎች ትብብርና የመሪነት ሚናም ኢትዮጵያ ላስመዘገበችው እመርታ ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከቱን አንስተዋል። በምክር ቤቱ የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አራሬ ሞሲሳ በበኩላቸው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ አዋጆች በማፅደቅ ጠንካራ የክትትልና ቁጥጥር የህዝብ ውክልና ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በዚህም ባለፉት ዓመታት በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ፕሮጀክቶች እንዲገነቡ በማስቻልና የከተማ ገፅታን በመቀየር በርካታ ስኬቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። የምክር ቤቱ አባል መስፍን እርካቤ፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ጥያቄና ችግሮች ምላሽ እያገኙ ምርታማነት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት የገጠሟትን የውስጥና የውጭ ፈተናዎች ተቋቁማ በሁሉም ዘርፎች የተሻለ ውጤት አስመዝግባለች ያሉት ደግሞ የምክር ቤቱ አባል የሆኑት አቡኔ አለም ናቸው። የምክር ቤት አባላቶቹ እየተከናወኑ የሚገኙት ውጤታማ የልማት ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ገልጸዋል።
የህወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ሃይሎች በወጣቶች ላይ የሚያካሂዱት አፈሳ እኩይ ድርጊት ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Jul 7, 2026 101
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የህወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ኃይሎች ወጣቶችን ከየትምህርት፣ ከሃይማኖት እና ከመንገድ ላይ በጉልበት እየተካሄደ ያለው አፈሳ ሰብኣዊነት የጎደለው እኩይ ድርጊት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። ሴንተር ፎር ሪስፖንሲብል ኤንድ ፒስፉል ፖለቲካ (CRPP) ከትግራይ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (TBS) ጋር በመተባበር ”ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት በትግራይ፡ የብዙኃን መገናኛ እና የማኅበረሰብ አንቂዎች ሚና” በሚል ርዕስ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮናታን ተስፋዬ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ጋዜጠኞችና የማኅበረሰብ አንቂዎች ተገኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ አሁን ጊዜው የትግራይን ሰላም ማዕከል አድርጎ በቁርጠኝነት መሥራት የሚያስፈልግበት ወቅት ነው ብለዋል። በሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች የሚታዩ የልማት እንቅስቃሴዎች በትግራይም መከናወን እንዳለባቸው አመልክተው፤ ሰላም ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በጥቂት አካላት በሚንቀሳቀሱ የሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮች ምክንያት ጠንካራውና ታታሪው የትግራይ ሕዝብ በልማት እንቅስቃሴዎች ውስጥ መሳተፍ አለመቻሉ እጅግ የሚያሳዝን መሆኑን ገልጸዋል። የሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ኃይሎች የክልሉን ሕዝብ ለዳግም ጥፋትና ስቃይ ለመዳረግ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንን ሁኔታ መላው ኅብረተሰብ በጋራና በአንድ ድምፅ በመቆም ሊቀለብሰው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አመራሩን ሳይቀር ከሞት ያዳኑ ወጣቶች ሰላም ሊሰፍን ይገባል ብለው ባመኑበት ወቅት፤ ከየትምህርት ቤቱ፣ ከየገዳማቱ፣ ከቤተክርስቲያንና ከመስጊዱ በጉልበት እየታፈሱ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮናታን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት የሚሰራጩ መረጃዎች በተለይም ከተለያዩ አካባቢዎች ድምፅ ለሚሆኑ ዜጎች የሚቀርቡ ዘገባዎች ጊዜውንና ሁኔታውን ያገናዘቡ መሆን እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። አሁን የሚፈልገው ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን ያገናዘቡና የሀገሪቱን እንዲሁም የቀጣናውን ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት ያስገቡ መሆን እንዳለባቸው ገልጸዋል። ሴንተር ፎር ሪስፖንሲብል ኤንድ ፒስፉል ፖለቲካ ጄነራል ማናጀር ሳሙኤል አባተ እንዳሉት፤ ሁሉም የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች፣ የማኅበረሰብ አንቂዎች የተሰጧቸውን መድረኮች በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል። ወጣቶችን ወደ ሌላ የስቃይ አዙሪት የሚገፋፋ ማንኛውንም ዓይነት መልዕክት በፅኑ መቃወም እንደሚገባ ገልጸዋል። ለእርቅ፣ ለእውነት፣ ለዴሞክራሲያዊ ተሳትፎና ሕዝብን ማዕከል ላደረገ ልማት የድርሻቸውን ማበርከት እንዳለባቸው አስታውቀዋል።
ማኅበሩ ተደራሽነቱን በማስፋት የሰብአዊ አገልግሎት ተግባራትን ይበልጥ ያጠናክራል
Jul 7, 2026 111
ጋምቤላ ፤ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ) ፡-የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ተደራሽነቱን በማስፋት እያከናወናቸው ያሉትን የሰብአዊ አገልግሎት ስራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። በማኅበሩ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት 17ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በጋምቤላ ከተማ አካሄዷል። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የቅርንጫፍ ጉዳዮችና ሎካላይዜሽን ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ መሐመድ ጀማል በጉባኤው ላይ እንዳሉት፣ ማኅበሩ ተደራሽነቱን ይበልጥ በማስፋት የተጠናከረ የሰብአዊ አገልግሎት ተግባሩን ለመወጣት ትኩረት ሰጥቷል። ማኅበሩ ካሉት ከ7 ሚሊዮን በላይ አባላቱ መዋጮ በመሰብሰብ በሚያጋጥሙ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ላይ ቀድሞ በመድረስ ለዜጎች ሰብአዊ ድጋፎችን እየሰጠ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በተጨማሪም ማኅበሩ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ800 በላይ አምቡላንሶችና ከ90 በላይ መድኃኒት ቤቶች አማካኝነት ለማኅበረሰቡ ሰብአዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም መንግሥት የሰብአዊ ድጋፎችን በራስ አቅም ለመሸፈን ለያዘው ግብ መሳካት ማኅበሩ የድርሻውን ለመወጣት በትኩረት እየሠራ መሆኑን ዋና ፀሐፊው ተናግረዋል። የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ ኢንጂነር ማክበዲ ኡቻን በጉባኤው ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ማህበሩ በአስቸጋሪ ወቅቶችና ፈተናዎች ወቅት ቀድሞ በመገኘት ያለ ምንም ልዩነት ለዜጎች ሰብአዊ ድጋፎችንና አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በክልሉ በተለያዩ ጊዜያት በሚያጋጥሙ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ችግሮች ላይ ቀድሞ በመድረስ ሲሰጥ ለቆየው በርካታ የሰብአዊ ድጋፍና አገልግሎት የክልሉ መንግሥት ምስጋናውን ይገልፃል ብለዋል። ተወካዩ አክለውም ማኅበሩ በቀጣይም የጀመራቸውን በጎ ተግባራት በተሻለ ሁኔታ ሊቀጥል እንደሚገባ ጠቁመው፣ ለሥራዎቹ መሳካት የክልሉ መንግሥት ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ማኅበሩ በነበረው የአንድ ቀን ጠቅላላ ጉባኤ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱን የአራት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጦ፣ ውይይት ካደረገበት በኋላ አፅድቋል። ጠቅላላ ጉባኤው በየአራት ዓመቱ በሚያካሄደው አዲስ የቦርድ አባላት ምርጫ መሠረት፣ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱን ለቀጣይ አራት ዓመታት የሚመሩ ሰባት የቦርድ አባላትን በመምረጥ ጉባኤው ተጠናቋል።
ፖለቲካ
የህወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ሃይሎች በወጣቶች ላይ የሚያካሂዱት አፈሳ እኩይ ድርጊት ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Jul 7, 2026 101
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የህወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ኃይሎች ወጣቶችን ከየትምህርት፣ ከሃይማኖት እና ከመንገድ ላይ በጉልበት እየተካሄደ ያለው አፈሳ ሰብኣዊነት የጎደለው እኩይ ድርጊት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። ሴንተር ፎር ሪስፖንሲብል ኤንድ ፒስፉል ፖለቲካ (CRPP) ከትግራይ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (TBS) ጋር በመተባበር ”ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት በትግራይ፡ የብዙኃን መገናኛ እና የማኅበረሰብ አንቂዎች ሚና” በሚል ርዕስ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮናታን ተስፋዬ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ጋዜጠኞችና የማኅበረሰብ አንቂዎች ተገኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ አሁን ጊዜው የትግራይን ሰላም ማዕከል አድርጎ በቁርጠኝነት መሥራት የሚያስፈልግበት ወቅት ነው ብለዋል። በሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች የሚታዩ የልማት እንቅስቃሴዎች በትግራይም መከናወን እንዳለባቸው አመልክተው፤ ሰላም ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በጥቂት አካላት በሚንቀሳቀሱ የሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮች ምክንያት ጠንካራውና ታታሪው የትግራይ ሕዝብ በልማት እንቅስቃሴዎች ውስጥ መሳተፍ አለመቻሉ እጅግ የሚያሳዝን መሆኑን ገልጸዋል። የሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ኃይሎች የክልሉን ሕዝብ ለዳግም ጥፋትና ስቃይ ለመዳረግ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንን ሁኔታ መላው ኅብረተሰብ በጋራና በአንድ ድምፅ በመቆም ሊቀለብሰው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አመራሩን ሳይቀር ከሞት ያዳኑ ወጣቶች ሰላም ሊሰፍን ይገባል ብለው ባመኑበት ወቅት፤ ከየትምህርት ቤቱ፣ ከየገዳማቱ፣ ከቤተክርስቲያንና ከመስጊዱ በጉልበት እየታፈሱ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮናታን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት የሚሰራጩ መረጃዎች በተለይም ከተለያዩ አካባቢዎች ድምፅ ለሚሆኑ ዜጎች የሚቀርቡ ዘገባዎች ጊዜውንና ሁኔታውን ያገናዘቡ መሆን እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። አሁን የሚፈልገው ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን ያገናዘቡና የሀገሪቱን እንዲሁም የቀጣናውን ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት ያስገቡ መሆን እንዳለባቸው ገልጸዋል። ሴንተር ፎር ሪስፖንሲብል ኤንድ ፒስፉል ፖለቲካ ጄነራል ማናጀር ሳሙኤል አባተ እንዳሉት፤ ሁሉም የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች፣ የማኅበረሰብ አንቂዎች የተሰጧቸውን መድረኮች በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል። ወጣቶችን ወደ ሌላ የስቃይ አዙሪት የሚገፋፋ ማንኛውንም ዓይነት መልዕክት በፅኑ መቃወም እንደሚገባ ገልጸዋል። ለእርቅ፣ ለእውነት፣ ለዴሞክራሲያዊ ተሳትፎና ሕዝብን ማዕከል ላደረገ ልማት የድርሻቸውን ማበርከት እንዳለባቸው አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያና ሩሲያ ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን ወደ ላቀ የትብብር ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ
Jul 7, 2026 128
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና ሩሲያ ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን ወደ ላቀ የትብብር ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያ ፌዴሬሽን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ውይይቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፥ ሚኒስትሮቹ በሁለትዮሽና በባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ትብብር መስኮች ላይ መክረዋል። በውይይቱ በዋናነት ከተነሱት ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚና የንግድ ትስስርን ማሳደግ አንዱ መሆኑን አስታውቀዋል። በተለይም የኢትዮጵያን የቡና ኤክስፖርት ማሳደግና ከሩሲያ የሚመጣውን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በትብብር ለመሥራት መስማማታቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም በኢንቨስትመንት፣ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ፍላጎት ማረጋገጣቸውንም አስረድተዋል። በዲፕሎማሲው ረገድም ኢትዮጵያ በብሪክስ (BRICS) አባልነቷ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት መድረኮች ላይ ከሩሲያ ጋር የምታደርገውን የውጭ ፖሊሲ ቅንጅት ይበልጥ ለማጎልበት ውይይት መደረጉን ጠቅሰዋል። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ትናንት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል።
የአፍሪካ ህብረትና ሩሲያ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ ትብብራቸውን ለማሳደግ ቁርጠኝነታቸውን አረጋገጡ
Jul 7, 2026 106
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ሩሲያ የጋራ ጥቅምን ማዕከል ባደረገ መልኩ፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አስታወቁ። ዓመታዊው የአፍሪካ ህብረት እና ሩሲያ የከፍተኛ ደረጃ ምክክር ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሂዷል። በምክክሩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና ልዑካን ቡድናቸው ተሳትፈዋል። ውይይቱ በጋራ መከባበር፣ በሉዓላዊ እኩልነትና በጋራ ጥቅሞች ላይ የተገነባውን፣ እንዲሁም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የአፍሪካ እና የሩሲያን አጋርነት ይበልጥ ያጸና መሆኑ ተመላክቷል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን እና አጀንዳ 2063ን በተጨባጭ መደገፍ የሚያስችሉ ቁልፍ የትብብር መስኮች ላይ ምክክር ተደርጓል። በዚህም መሠረት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ መሠረተ ልማትና ኢነርጂ ልማት ላይ ከመተባበር ባለፈ፤ በቴክኖሎጂ፣ በምግብ ዋስትና፣ በማህበረሰብ ጤና እና በኢንዱስትሪ ሽግግር ዙሪያ ያሉ ስትራቴጂካዊ አጋርነቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር የሚያስችል አቅጣጫ ተቀምጧል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ሩሲያ በአፍሪካ ያላትን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲሁም በሰብዓዊ ድጋፍ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ ምግብ ዋስትና እና አቅም ግንባታ አስመልክቶ እያደረገች ያለውን ዘለቄታዊ ድጋፍ አድንቀዋል። በተጨማሪም በሰላም እና ደህንነት፣ በአፍሪካ-መር የግጭት አፈታት መፍትሄዎች፣ በአፍሪካ ህብረት እና በተመድ መካከል ያለውን የሰላምና ጸጥታ ትብብር ማጠናከርን ያለመው የፀጥታው ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ 2719 አፈፃፀምና በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ አፍሪካ ሙሉ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ያላቸው ሁለት ቋሚና አምስት ቋሚ ያልሆኑ መቀመጫዎች እንዲኖሯት የሚጠይቅ የአፍሪካ ኅብረት የጋራ የፖሊሲ አቋም (Ezulwini Consensus) ዙሪያም ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። የባለብዙ ወገን ትብብርን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም መክረዋል። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ የአፍሪካን ቋሚ ውክልና ጨምሮ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ይበልጥ አሳታፊ እና ፍትሃዊ እንዲሆን እየተደረገ ላለው ጥረት ድጋፏን ማድረግ እንደምትቀጥል አመልክተዋል። ላቭሮቭ ለአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት አድናቆት የቸሩ ሲሆን፣ የአህጉሪቱ የግብርና እና የማዕድን ምርቶች ላይ እሴት መጨመር አለበት በማለት ሊቀመንበሩ ላቀረቡት ጥሪም አጋርነታቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ ሰብዓዊ ኤጀንሲንና የአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲን ጨምሮ የአፍሪካ ህብረትን ተቋማዊ አቅም ለማጠናከር ሩሲያ ድጋፏን እንደምታደርግ ተናግረዋል። ሁለቱ መሪዎች የአፍሪካ ህብረት እና የሩሲያን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ እንዲሁም በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም የሚካሄደው 3ኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ዝግጅት ስኬታማ እንዲሆን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት መግለጻቸውን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል።
በምክር ቤት የነበራቸውን ቆይታ ያጠናቀቁ አባላት ከመንግሥት ጋር በመሆን ኢትዮጵያን ለማገልገል ሊሰሩ ይገባል
Jul 7, 2026 161
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነበራቸውን ቆይታ ያጠናቀቁ አባላት፣ ከመንግሥት ጋር በመሆን ኢትዮጵያን የማገልገልና ሀገርን በጋራ የማልማት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በመገኘት የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው ወቅት፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በምክር ቤቱ ከፍተኛ ሀገራዊ አገልግሎት ሲያበረክቱ ለቆዩና በሚቀጥለው የምክር ቤት ዘመን ለማይቀጥሉ የብልፅግና ፓርቲም ሆነ የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት እንዲሁም የግል ተወዳዳሪዎች በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት ሕዝብና መንግሥትን በታማኝነት ሲያገለግሉ የቆዩና የምክር ቤት የስራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ የብልፅግና ፓርቲ አባላት በፓርቲና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በተለያየ ደረጃ አገልግሎታቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ድርጅቱና መንግሥት የላቀ ምስጋና እና ክብር ያቀርብላችኋል ሲሉም ገልጸዋል። አባላቱ ባለፉት አምስት ዓመታት በእውቀታቸውና በአቅማቸው ልክ ሀገራቸውን ማገልገላቸውንና በምክር ቤቱ ውስጥ የሕዝብን ድምፅ ማሰማታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና የግል ተወዳዳሪዎችም ባለፉት አምስት ዓመታት በምክር ቤት ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው፤ በምርጫው ውጤት መሠረት በአዲሱ ምክር ቤት የማይቀጥሉ አባላት በምክር ቤት ቆይታቸው ማብቂያ ሀገራዊ አገልግሎታቸውን የሚያቆሙበት ሊሆን እንደማይገባ አስገንዝበዋል። ከምክር ቤት ውጪ ከመንግሥት ጋር ሆነው ኢትዮጵያን እንዲያገለግሉ ጥሪ ያቀረቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት እነርሱን አካቶ ኢትዮጵያን ማልማት እንደሚፈልግም ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሁሉም የጋራ ሀገር መሆኗን ጠቁመው፤ ትብብሩ በምክር ቤት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን በተለያዩ ዘርፎች ሊቀጥል እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በምክር ቤት ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ዘርፎች ተባብሮ ኢትዮጵያን ማበልጸግ እንደሚገባ ጠቁመው፤ አብረን እንስራ ሲሉ ጥሪ በማቅረብ አብሮ የመሥራት ጉዟቸው መቋጫ እንዳይኖረው ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል የለም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 7, 2026 279
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል የለም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዲፕሎማሲው ዘርፍና በቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው፤ ኢትዮጵያ በመቋቋም፣ በመጠቀምና በመግራት የዲፕሎማሲ መርሆች አማካኝነት ብሔራዊ ጥቅሟን በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያስጠብቅ አቅም መገንባቷን አብራርተዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ጠላቶች ከሀገሪቱ ፍላጎቶችና ብሔራዊ ጥቅሞች በተጻራሪ የሆኑ፣ በሦስት 'መ'ዎች ላይ የተመሰረቱ ስሁት መርሆችንና ስሌቶችን እየተከተሉ መሆኑን አስረድተዋል። መካድ፦ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብት ያላት፣ አልገዛም የሚል ሕዝብ ያላት፣ ሊገዟት ብዙ ጊዜ ሞክረው ተሸንፈው የተመለሱባት ሀገር መሆኗንና ሀገሪቱን ማንበርከክ ቀላል አለመሆኑን ታሪክ ቢያውቅም፤ ጠላቶቿ ግን ይህንን እውነት ይክዳሉ ብለዋል። መርሳት፦ ጠላቶች በዚህ ስሁት መንገዳቸው ይህቺ ሀገር ስትራቴጂካዊ ጥልቀት ያላት፣ የሰብዓዊ ኃይል ትርፍ ያላትና የወጣቶች ሀገር መሆኗን፣ እንዲሁም በክፉ ጊዜ ራሷን መከላከል እንደምትችል ይረሳሉ ነው ያሉት። የሀገሪቱ አቀማመጥና ተቋማዊ ልምምዱ ቀላል አለመሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጠላቶች ይህንን በመርሳት ስሁት ስሌት ውስጥ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል። በዚህም ምክንያት ስለ እኛ ሲያስቡ ድህነታችንን እንጂ እምቢ ባይነታችንን ማስታወስ እንደማይፈልጉና አንዳንዴም ማራከስ እንደሚሹ አንስተዋል። ምኞት፦ የዚህ ጊዜ ያለፈበት ስልትና ምኞት እስረኛ መሆንም ሌላኛው የጠላቶች ስሁት ስሌት መሆኑን አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ማጠቃለያ፤ የትኛውም የሀገር ውስጥ ባንዳና የውጭ ጠላት ቢተባበር እንኳ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት እንደሌለ በአስተማማኝ ሁኔታ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ በመቋቋም፣ በመጠቀምና መግራት የዲፕሎማሲ መርህ ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቅ አቅም ገንብታለች
Jul 7, 2026 270
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በመቋቋም፣ በመጠቀምና መግራት የዲፕሎማሲ መርህ ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቅ አቅም ገንብታለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዲፕሎማሲው ዘርፍና በቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ በመቋቋም፣ በመጠቀምና መግራት የዲፕሎማሲ መርህ ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቅ አቅም ገንብታለች ብለዋል። ዓለም በአሁኑ ወቅት በጣም ተለዋዋጭ፣ ኢ-ተገማችና በብዙ ዘርፎች ውስብስብ ባህሪ ይዟል ነው ያሉት። በዚህ ውስብስብ፣ ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነ አውድ ውስጥ በቋሚነት አንድ ወጥ መርህ ብቻ ማስቀመጥ እንደሚያስቸግር ጠቁመው፤ ዋናው መስፈሪያ ብሔራዊ ጥቅምን ያማከለና ገቢር-ነክ (ተግባር ተኮር) የሆነ የዲፕሎማሲ አካሄድ መከተል እንደሆነ ገልጸዋል። የእኛ መርህ የኢትዮጵያን የውሳኔ ሉዓላዊነት ማስጠበቅ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ስኬት በኢትዮጵያ የብሔራዊ ጥቅም ውሳኔዎች ውስጥ ሌሎች አካላት ተፅዕኖ እንዲያደርጉ አለመፍቀድ ቀዳሚ ተግባር መሆኑንም አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ በቀላሉ ሸብረክ የምትል ሀገር እንዳልሆነች በማንሳትም፤ በዓለም የዲፕሎማሲ ሒደት ውስጥ ሀገሪቱ የምትከተለው መርህ በሦስት 'መ'ዎች ላይ የተመሰረተ መሆኑን አስረድተዋል። እነርሱም መቋቋም፦ ጠንካራ ተቋምና ሀገር መፍጠር፤ መጠቀም፦ የሚገጥሙ ፈተናዎችን ወደ መልካም ዕድል መቀየር፤ እንዲሁም መግራት፦ በሌሎች አካላት አጀንዳ ከመመራት ይልቅ የራስን አጀንዳ ቀርጾ መግራት መቻል ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ በእነዚህ በመቋቋም፣ በመጠቀምና በመግራት የዲፕሎማሲ መርሆች አማካኝነት ብሔራዊ ጥቅሟን በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያስጠብቅ አቅም መገንባቷን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰፊው አብራርተዋል።
ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናከረ ውይይት ብቻ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 7, 2026 256
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናከረ ውይይት ብቻ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና መረጋጋትን በተመለከት በሰጡት በምላሽ እና ማብራሪያ ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናከረ ውይይት ብቻ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ አለመረጋጋቶችን ለመፍታት መንግሥት ከ4000 በላይ የምክክር መድረኮችንና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በማሳተፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁን የብሔራዊ መግባባት ምእራፍ ተሻግረናል ሲሉ ገልጸዋል። ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናከረ ውይይት ብቻ ነው ሲሉም በምላሻቸው አክለዋል።
የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደ ተራ የድርድር ሂደት ብቻ ሳይሆን፣ በርካታ ተጨባጭ ውጤቶችን ያስገኘ ታላቅ የሰላም ውጥን ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል
Jul 7, 2026 248
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደ ተራ የድርድር ሂደት ብቻ ሳይሆን፣ በርካታ ተጨባጭ ውጤቶችን ያስገኘ ታላቅ የሰላም ውጥን ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 30ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት የፕሪቶሪያ ስምምነትን በተመለከተ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። በምላሻቸውም የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደ ተራ የድርድር ሂደት ብቻ ሳይሆን፣ በርካታ ተጨባጭ ውጤቶችን ያስገኘ ታላቅ የሰላም ውጥን ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል ብለዋል። ከሁሉ በላይ ደግሞ አሸናፊና ተሸናፊ ወገኖች በእኩልነት ቁጭ ብለው የተወያዩበት መድረክ ነበር ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለዋል። መንግስት ወታደራዊ የበላይነት ከጨበጠ በኋላ የተሸነፈውን አካል በጠረጴዛ ዙሪያ አስቀምጦ መደራደርና መፈራረም ብቻ ሳይሆን፣ በችግር ውስጥ የነበሩ የታጠቁ ኃይሎችን ቀርቦ በመደገፍ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር አሳይቷል ነው ያሉት። በዚህ ስምምነት ምን ተገኘ ለሚሉ ወገኖች ቢያንስ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም መቻሉን እንደ ትልቅ ስኬት ማንሳት ይቻላል ብለዋል። በተጨማሪም ከ60 ሺህ ያላነሱ ታጣቂዎች የዲዲአር (DDR) ክፍያ ተፈጽሞላቸው ከሰራዊቱ እንዲቀነሱ የተደረገ ሲሆን፣ በርካታ እስረኞችና ምርኮኞችም ተፈተዋል ነው ያሉት በማብራሪያቸው።
ፖለቲካ
የህወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ሃይሎች በወጣቶች ላይ የሚያካሂዱት አፈሳ እኩይ ድርጊት ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Jul 7, 2026 101
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የህወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ኃይሎች ወጣቶችን ከየትምህርት፣ ከሃይማኖት እና ከመንገድ ላይ በጉልበት እየተካሄደ ያለው አፈሳ ሰብኣዊነት የጎደለው እኩይ ድርጊት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ። ሴንተር ፎር ሪስፖንሲብል ኤንድ ፒስፉል ፖለቲካ (CRPP) ከትግራይ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (TBS) ጋር በመተባበር ”ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት በትግራይ፡ የብዙኃን መገናኛ እና የማኅበረሰብ አንቂዎች ሚና” በሚል ርዕስ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮናታን ተስፋዬ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ጋዜጠኞችና የማኅበረሰብ አንቂዎች ተገኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ አሁን ጊዜው የትግራይን ሰላም ማዕከል አድርጎ በቁርጠኝነት መሥራት የሚያስፈልግበት ወቅት ነው ብለዋል። በሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች የሚታዩ የልማት እንቅስቃሴዎች በትግራይም መከናወን እንዳለባቸው አመልክተው፤ ሰላም ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በጥቂት አካላት በሚንቀሳቀሱ የሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮች ምክንያት ጠንካራውና ታታሪው የትግራይ ሕዝብ በልማት እንቅስቃሴዎች ውስጥ መሳተፍ አለመቻሉ እጅግ የሚያሳዝን መሆኑን ገልጸዋል። የሕወሃት ጽንፈኛ አመራሮችና የጥፋት ኃይሎች የክልሉን ሕዝብ ለዳግም ጥፋትና ስቃይ ለመዳረግ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንን ሁኔታ መላው ኅብረተሰብ በጋራና በአንድ ድምፅ በመቆም ሊቀለብሰው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አመራሩን ሳይቀር ከሞት ያዳኑ ወጣቶች ሰላም ሊሰፍን ይገባል ብለው ባመኑበት ወቅት፤ ከየትምህርት ቤቱ፣ ከየገዳማቱ፣ ከቤተክርስቲያንና ከመስጊዱ በጉልበት እየታፈሱ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮናታን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት የሚሰራጩ መረጃዎች በተለይም ከተለያዩ አካባቢዎች ድምፅ ለሚሆኑ ዜጎች የሚቀርቡ ዘገባዎች ጊዜውንና ሁኔታውን ያገናዘቡ መሆን እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። አሁን የሚፈልገው ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን ያገናዘቡና የሀገሪቱን እንዲሁም የቀጣናውን ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት ያስገቡ መሆን እንዳለባቸው ገልጸዋል። ሴንተር ፎር ሪስፖንሲብል ኤንድ ፒስፉል ፖለቲካ ጄነራል ማናጀር ሳሙኤል አባተ እንዳሉት፤ ሁሉም የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች፣ የማኅበረሰብ አንቂዎች የተሰጧቸውን መድረኮች በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል። ወጣቶችን ወደ ሌላ የስቃይ አዙሪት የሚገፋፋ ማንኛውንም ዓይነት መልዕክት በፅኑ መቃወም እንደሚገባ ገልጸዋል። ለእርቅ፣ ለእውነት፣ ለዴሞክራሲያዊ ተሳትፎና ሕዝብን ማዕከል ላደረገ ልማት የድርሻቸውን ማበርከት እንዳለባቸው አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያና ሩሲያ ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን ወደ ላቀ የትብብር ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ
Jul 7, 2026 128
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና ሩሲያ ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን ወደ ላቀ የትብብር ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያ ፌዴሬሽን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ውይይቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፥ ሚኒስትሮቹ በሁለትዮሽና በባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ትብብር መስኮች ላይ መክረዋል። በውይይቱ በዋናነት ከተነሱት ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚና የንግድ ትስስርን ማሳደግ አንዱ መሆኑን አስታውቀዋል። በተለይም የኢትዮጵያን የቡና ኤክስፖርት ማሳደግና ከሩሲያ የሚመጣውን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በትብብር ለመሥራት መስማማታቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም በኢንቨስትመንት፣ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ፍላጎት ማረጋገጣቸውንም አስረድተዋል። በዲፕሎማሲው ረገድም ኢትዮጵያ በብሪክስ (BRICS) አባልነቷ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት መድረኮች ላይ ከሩሲያ ጋር የምታደርገውን የውጭ ፖሊሲ ቅንጅት ይበልጥ ለማጎልበት ውይይት መደረጉን ጠቅሰዋል። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ትናንት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል።
የአፍሪካ ህብረትና ሩሲያ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ ትብብራቸውን ለማሳደግ ቁርጠኝነታቸውን አረጋገጡ
Jul 7, 2026 106
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ሩሲያ የጋራ ጥቅምን ማዕከል ባደረገ መልኩ፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አስታወቁ። ዓመታዊው የአፍሪካ ህብረት እና ሩሲያ የከፍተኛ ደረጃ ምክክር ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሂዷል። በምክክሩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና ልዑካን ቡድናቸው ተሳትፈዋል። ውይይቱ በጋራ መከባበር፣ በሉዓላዊ እኩልነትና በጋራ ጥቅሞች ላይ የተገነባውን፣ እንዲሁም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የአፍሪካ እና የሩሲያን አጋርነት ይበልጥ ያጸና መሆኑ ተመላክቷል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን እና አጀንዳ 2063ን በተጨባጭ መደገፍ የሚያስችሉ ቁልፍ የትብብር መስኮች ላይ ምክክር ተደርጓል። በዚህም መሠረት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ መሠረተ ልማትና ኢነርጂ ልማት ላይ ከመተባበር ባለፈ፤ በቴክኖሎጂ፣ በምግብ ዋስትና፣ በማህበረሰብ ጤና እና በኢንዱስትሪ ሽግግር ዙሪያ ያሉ ስትራቴጂካዊ አጋርነቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር የሚያስችል አቅጣጫ ተቀምጧል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ሩሲያ በአፍሪካ ያላትን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲሁም በሰብዓዊ ድጋፍ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ ምግብ ዋስትና እና አቅም ግንባታ አስመልክቶ እያደረገች ያለውን ዘለቄታዊ ድጋፍ አድንቀዋል። በተጨማሪም በሰላም እና ደህንነት፣ በአፍሪካ-መር የግጭት አፈታት መፍትሄዎች፣ በአፍሪካ ህብረት እና በተመድ መካከል ያለውን የሰላምና ጸጥታ ትብብር ማጠናከርን ያለመው የፀጥታው ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ 2719 አፈፃፀምና በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ አፍሪካ ሙሉ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ያላቸው ሁለት ቋሚና አምስት ቋሚ ያልሆኑ መቀመጫዎች እንዲኖሯት የሚጠይቅ የአፍሪካ ኅብረት የጋራ የፖሊሲ አቋም (Ezulwini Consensus) ዙሪያም ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። የባለብዙ ወገን ትብብርን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም መክረዋል። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ የአፍሪካን ቋሚ ውክልና ጨምሮ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ይበልጥ አሳታፊ እና ፍትሃዊ እንዲሆን እየተደረገ ላለው ጥረት ድጋፏን ማድረግ እንደምትቀጥል አመልክተዋል። ላቭሮቭ ለአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት አድናቆት የቸሩ ሲሆን፣ የአህጉሪቱ የግብርና እና የማዕድን ምርቶች ላይ እሴት መጨመር አለበት በማለት ሊቀመንበሩ ላቀረቡት ጥሪም አጋርነታቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ ሰብዓዊ ኤጀንሲንና የአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲን ጨምሮ የአፍሪካ ህብረትን ተቋማዊ አቅም ለማጠናከር ሩሲያ ድጋፏን እንደምታደርግ ተናግረዋል። ሁለቱ መሪዎች የአፍሪካ ህብረት እና የሩሲያን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ እንዲሁም በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም የሚካሄደው 3ኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ዝግጅት ስኬታማ እንዲሆን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት መግለጻቸውን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል።
በምክር ቤት የነበራቸውን ቆይታ ያጠናቀቁ አባላት ከመንግሥት ጋር በመሆን ኢትዮጵያን ለማገልገል ሊሰሩ ይገባል
Jul 7, 2026 161
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነበራቸውን ቆይታ ያጠናቀቁ አባላት፣ ከመንግሥት ጋር በመሆን ኢትዮጵያን የማገልገልና ሀገርን በጋራ የማልማት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በመገኘት የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው ወቅት፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በምክር ቤቱ ከፍተኛ ሀገራዊ አገልግሎት ሲያበረክቱ ለቆዩና በሚቀጥለው የምክር ቤት ዘመን ለማይቀጥሉ የብልፅግና ፓርቲም ሆነ የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት እንዲሁም የግል ተወዳዳሪዎች በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት ሕዝብና መንግሥትን በታማኝነት ሲያገለግሉ የቆዩና የምክር ቤት የስራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ የብልፅግና ፓርቲ አባላት በፓርቲና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በተለያየ ደረጃ አገልግሎታቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ድርጅቱና መንግሥት የላቀ ምስጋና እና ክብር ያቀርብላችኋል ሲሉም ገልጸዋል። አባላቱ ባለፉት አምስት ዓመታት በእውቀታቸውና በአቅማቸው ልክ ሀገራቸውን ማገልገላቸውንና በምክር ቤቱ ውስጥ የሕዝብን ድምፅ ማሰማታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና የግል ተወዳዳሪዎችም ባለፉት አምስት ዓመታት በምክር ቤት ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው፤ በምርጫው ውጤት መሠረት በአዲሱ ምክር ቤት የማይቀጥሉ አባላት በምክር ቤት ቆይታቸው ማብቂያ ሀገራዊ አገልግሎታቸውን የሚያቆሙበት ሊሆን እንደማይገባ አስገንዝበዋል። ከምክር ቤት ውጪ ከመንግሥት ጋር ሆነው ኢትዮጵያን እንዲያገለግሉ ጥሪ ያቀረቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት እነርሱን አካቶ ኢትዮጵያን ማልማት እንደሚፈልግም ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሁሉም የጋራ ሀገር መሆኗን ጠቁመው፤ ትብብሩ በምክር ቤት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን በተለያዩ ዘርፎች ሊቀጥል እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በምክር ቤት ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ዘርፎች ተባብሮ ኢትዮጵያን ማበልጸግ እንደሚገባ ጠቁመው፤ አብረን እንስራ ሲሉ ጥሪ በማቅረብ አብሮ የመሥራት ጉዟቸው መቋጫ እንዳይኖረው ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል የለም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 7, 2026 279
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል የለም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዲፕሎማሲው ዘርፍና በቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው፤ ኢትዮጵያ በመቋቋም፣ በመጠቀምና በመግራት የዲፕሎማሲ መርሆች አማካኝነት ብሔራዊ ጥቅሟን በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያስጠብቅ አቅም መገንባቷን አብራርተዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ጠላቶች ከሀገሪቱ ፍላጎቶችና ብሔራዊ ጥቅሞች በተጻራሪ የሆኑ፣ በሦስት 'መ'ዎች ላይ የተመሰረቱ ስሁት መርሆችንና ስሌቶችን እየተከተሉ መሆኑን አስረድተዋል። መካድ፦ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብት ያላት፣ አልገዛም የሚል ሕዝብ ያላት፣ ሊገዟት ብዙ ጊዜ ሞክረው ተሸንፈው የተመለሱባት ሀገር መሆኗንና ሀገሪቱን ማንበርከክ ቀላል አለመሆኑን ታሪክ ቢያውቅም፤ ጠላቶቿ ግን ይህንን እውነት ይክዳሉ ብለዋል። መርሳት፦ ጠላቶች በዚህ ስሁት መንገዳቸው ይህቺ ሀገር ስትራቴጂካዊ ጥልቀት ያላት፣ የሰብዓዊ ኃይል ትርፍ ያላትና የወጣቶች ሀገር መሆኗን፣ እንዲሁም በክፉ ጊዜ ራሷን መከላከል እንደምትችል ይረሳሉ ነው ያሉት። የሀገሪቱ አቀማመጥና ተቋማዊ ልምምዱ ቀላል አለመሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጠላቶች ይህንን በመርሳት ስሁት ስሌት ውስጥ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል። በዚህም ምክንያት ስለ እኛ ሲያስቡ ድህነታችንን እንጂ እምቢ ባይነታችንን ማስታወስ እንደማይፈልጉና አንዳንዴም ማራከስ እንደሚሹ አንስተዋል። ምኞት፦ የዚህ ጊዜ ያለፈበት ስልትና ምኞት እስረኛ መሆንም ሌላኛው የጠላቶች ስሁት ስሌት መሆኑን አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ማጠቃለያ፤ የትኛውም የሀገር ውስጥ ባንዳና የውጭ ጠላት ቢተባበር እንኳ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት እንደሌለ በአስተማማኝ ሁኔታ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ በመቋቋም፣ በመጠቀምና መግራት የዲፕሎማሲ መርህ ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቅ አቅም ገንብታለች
Jul 7, 2026 270
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በመቋቋም፣ በመጠቀምና መግራት የዲፕሎማሲ መርህ ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቅ አቅም ገንብታለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዲፕሎማሲው ዘርፍና በቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ በመቋቋም፣ በመጠቀምና መግራት የዲፕሎማሲ መርህ ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቅ አቅም ገንብታለች ብለዋል። ዓለም በአሁኑ ወቅት በጣም ተለዋዋጭ፣ ኢ-ተገማችና በብዙ ዘርፎች ውስብስብ ባህሪ ይዟል ነው ያሉት። በዚህ ውስብስብ፣ ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነ አውድ ውስጥ በቋሚነት አንድ ወጥ መርህ ብቻ ማስቀመጥ እንደሚያስቸግር ጠቁመው፤ ዋናው መስፈሪያ ብሔራዊ ጥቅምን ያማከለና ገቢር-ነክ (ተግባር ተኮር) የሆነ የዲፕሎማሲ አካሄድ መከተል እንደሆነ ገልጸዋል። የእኛ መርህ የኢትዮጵያን የውሳኔ ሉዓላዊነት ማስጠበቅ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ስኬት በኢትዮጵያ የብሔራዊ ጥቅም ውሳኔዎች ውስጥ ሌሎች አካላት ተፅዕኖ እንዲያደርጉ አለመፍቀድ ቀዳሚ ተግባር መሆኑንም አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ በቀላሉ ሸብረክ የምትል ሀገር እንዳልሆነች በማንሳትም፤ በዓለም የዲፕሎማሲ ሒደት ውስጥ ሀገሪቱ የምትከተለው መርህ በሦስት 'መ'ዎች ላይ የተመሰረተ መሆኑን አስረድተዋል። እነርሱም መቋቋም፦ ጠንካራ ተቋምና ሀገር መፍጠር፤ መጠቀም፦ የሚገጥሙ ፈተናዎችን ወደ መልካም ዕድል መቀየር፤ እንዲሁም መግራት፦ በሌሎች አካላት አጀንዳ ከመመራት ይልቅ የራስን አጀንዳ ቀርጾ መግራት መቻል ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ በእነዚህ በመቋቋም፣ በመጠቀምና በመግራት የዲፕሎማሲ መርሆች አማካኝነት ብሔራዊ ጥቅሟን በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያስጠብቅ አቅም መገንባቷን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰፊው አብራርተዋል።
ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናከረ ውይይት ብቻ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 7, 2026 256
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናከረ ውይይት ብቻ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና መረጋጋትን በተመለከት በሰጡት በምላሽ እና ማብራሪያ ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናከረ ውይይት ብቻ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ አለመረጋጋቶችን ለመፍታት መንግሥት ከ4000 በላይ የምክክር መድረኮችንና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በማሳተፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁን የብሔራዊ መግባባት ምእራፍ ተሻግረናል ሲሉ ገልጸዋል። ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናከረ ውይይት ብቻ ነው ሲሉም በምላሻቸው አክለዋል።
የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደ ተራ የድርድር ሂደት ብቻ ሳይሆን፣ በርካታ ተጨባጭ ውጤቶችን ያስገኘ ታላቅ የሰላም ውጥን ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል
Jul 7, 2026 248
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደ ተራ የድርድር ሂደት ብቻ ሳይሆን፣ በርካታ ተጨባጭ ውጤቶችን ያስገኘ ታላቅ የሰላም ውጥን ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 30ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት የፕሪቶሪያ ስምምነትን በተመለከተ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። በምላሻቸውም የፕሪቶሪያው ስምምነት እንደ ተራ የድርድር ሂደት ብቻ ሳይሆን፣ በርካታ ተጨባጭ ውጤቶችን ያስገኘ ታላቅ የሰላም ውጥን ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል ብለዋል። ከሁሉ በላይ ደግሞ አሸናፊና ተሸናፊ ወገኖች በእኩልነት ቁጭ ብለው የተወያዩበት መድረክ ነበር ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለዋል። መንግስት ወታደራዊ የበላይነት ከጨበጠ በኋላ የተሸነፈውን አካል በጠረጴዛ ዙሪያ አስቀምጦ መደራደርና መፈራረም ብቻ ሳይሆን፣ በችግር ውስጥ የነበሩ የታጠቁ ኃይሎችን ቀርቦ በመደገፍ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር አሳይቷል ነው ያሉት። በዚህ ስምምነት ምን ተገኘ ለሚሉ ወገኖች ቢያንስ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም መቻሉን እንደ ትልቅ ስኬት ማንሳት ይቻላል ብለዋል። በተጨማሪም ከ60 ሺህ ያላነሱ ታጣቂዎች የዲዲአር (DDR) ክፍያ ተፈጽሞላቸው ከሰራዊቱ እንዲቀነሱ የተደረገ ሲሆን፣ በርካታ እስረኞችና ምርኮኞችም ተፈተዋል ነው ያሉት በማብራሪያቸው።
ማህበራዊ
ማኅበሩ ተደራሽነቱን በማስፋት የሰብአዊ አገልግሎት ተግባራትን ይበልጥ ያጠናክራል
Jul 7, 2026 111
ጋምቤላ ፤ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ) ፡-የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ተደራሽነቱን በማስፋት እያከናወናቸው ያሉትን የሰብአዊ አገልግሎት ስራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። በማኅበሩ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት 17ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በጋምቤላ ከተማ አካሄዷል። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የቅርንጫፍ ጉዳዮችና ሎካላይዜሽን ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ መሐመድ ጀማል በጉባኤው ላይ እንዳሉት፣ ማኅበሩ ተደራሽነቱን ይበልጥ በማስፋት የተጠናከረ የሰብአዊ አገልግሎት ተግባሩን ለመወጣት ትኩረት ሰጥቷል። ማኅበሩ ካሉት ከ7 ሚሊዮን በላይ አባላቱ መዋጮ በመሰብሰብ በሚያጋጥሙ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ላይ ቀድሞ በመድረስ ለዜጎች ሰብአዊ ድጋፎችን እየሰጠ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በተጨማሪም ማኅበሩ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ800 በላይ አምቡላንሶችና ከ90 በላይ መድኃኒት ቤቶች አማካኝነት ለማኅበረሰቡ ሰብአዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም መንግሥት የሰብአዊ ድጋፎችን በራስ አቅም ለመሸፈን ለያዘው ግብ መሳካት ማኅበሩ የድርሻውን ለመወጣት በትኩረት እየሠራ መሆኑን ዋና ፀሐፊው ተናግረዋል። የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ ኢንጂነር ማክበዲ ኡቻን በጉባኤው ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ማህበሩ በአስቸጋሪ ወቅቶችና ፈተናዎች ወቅት ቀድሞ በመገኘት ያለ ምንም ልዩነት ለዜጎች ሰብአዊ ድጋፎችንና አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በክልሉ በተለያዩ ጊዜያት በሚያጋጥሙ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ችግሮች ላይ ቀድሞ በመድረስ ሲሰጥ ለቆየው በርካታ የሰብአዊ ድጋፍና አገልግሎት የክልሉ መንግሥት ምስጋናውን ይገልፃል ብለዋል። ተወካዩ አክለውም ማኅበሩ በቀጣይም የጀመራቸውን በጎ ተግባራት በተሻለ ሁኔታ ሊቀጥል እንደሚገባ ጠቁመው፣ ለሥራዎቹ መሳካት የክልሉ መንግሥት ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ማኅበሩ በነበረው የአንድ ቀን ጠቅላላ ጉባኤ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱን የአራት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጦ፣ ውይይት ካደረገበት በኋላ አፅድቋል። ጠቅላላ ጉባኤው በየአራት ዓመቱ በሚያካሄደው አዲስ የቦርድ አባላት ምርጫ መሠረት፣ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱን ለቀጣይ አራት ዓመታት የሚመሩ ሰባት የቦርድ አባላትን በመምረጥ ጉባኤው ተጠናቋል።
ከአገልግሎት ዘርፍ 9 ነጥብ 8 በመቶው ዕድገት ይጠበቃል
Jul 7, 2026 142
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ የአገልግሎት ዘርፍ 9 ነጥብ 8 በመቶው ዕድገት እንደሚጠበቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማብራሪያቸው፤ የኢትዮጵያ የአገልግሎት ዘርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ መጠን እያደገ መምጣቱን አመላክተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በአዲስ አበባ ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች መካሔዳቸውን ጠቅሰው በነዚህ ስብሰባዎች ለሚሳተፉ አካላት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰፊ የማጓጓዝ አገልግሎት መስጠቱን ጠቁመዋል፡፡ የዓለም አቀፍ ስብሰባው ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚያገኙት ከሆቴሎች መሆኑን አንስተዋል፡፡ የአገልግሎት ዘርፍ 9 ነጥብ 8 በመቶ ዕድገት እንደሚጠበቅም ጠቅሰው ዘርፉ ከፍተኛ የስራ እድል አማራጭ እየሆነ መምጣቱንም እንዲሁ፡፡
የኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ የሕክምና አገልግሎት የመስጠት አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ተሸጋግሯል
Jul 7, 2026 132
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ የሕክምና አገልግሎት የመስጠት አቅም ወደ ላቀ ደረጃ መሸጋገሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጤናው ዘርፍ በሰጡት ማብራሪያ፤ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረት አቅም ከነበረበት 4 በመቶ አሁን ላይ ወደ 44 በመቶ ማደግ እንደቻለ ገልጸዋል። ለአጠቃላይ መድኃኒት ግዢ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለሕክምና መሣሪያዎች ግዢ ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉም ጤናውን ዘርፍ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የተደረገ ውጤት መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ወራት በርካታ ሆስፒታሎችን ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውና በሚቀጥሉት ወራት የሚመረቁ ሌሎች ተቋማት መኖራቸውም የጤናውን ዘርፍ እመርታዊ ውጤት እንደሚያሳይ አንስተዋል። ለአብነትም ለግንባታ ሂደት ትኩረት ከተሰጣቸው መካከል የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልን የአልጋ አቅም በአንድ ሺህ ያሳደገው አዲሱ ሕንፃ ተምሳሌት መሆኑን አስረድተዋል። በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ተደርገውእየተሰሩ እንደሚገኝም አብራርተዋል። በቀጣይም በውጭ ሀገራት የሚታዩ ዘመናዊና ደረጃቸውን የጠበቁ ሆስፒታሎችን በኢትዮጵያ መገንባት መሆኑም አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል የወባ በሽታን ለመቀነስ በተደረገው የተቀናጀ ጥረት 14 ሚሊዮን አጎበር የተሰራጨ ሲሆን፣ በ3 ሚሊዮን መኖሪያ ቤቶች ላይ ደግሞ የጸረ-ወባ ኬሚካል የእርጭት መርሃ ግብር መካሄዱን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም፣ ቀደም ሲል የክትባት ተደራሽነት ባልነበረባቸው 58 ወረዳዎች ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ክትባት መስጠት መቻሉን አስታውቀዋል። መንግስት የጤናው ዘርፍ የህክምና አገልግሎት የመስጠት አቅሙን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ እስፈላጊ ልማቶችን ለማስፋፋት የሰራቸው ተግባራት አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን አስረድተዋል።
የትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 7, 2026 179
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትምህርት ዘርፍ ጥራት እና ለውጦችን በተመለከተ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ የትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው ፈተና የሚወስዱበት አሰራር መተግበሩን ጠቁመው በዚህም የኩራጃ ባህልን ማስረቀት ተችሏል ነው ያሉት። ትምህርት ከታች ካልተሠራ ከላይ መሥራት ውጤታማ አያደርግም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለመዋዕለ ህጻናት ማስፋፊያ በተሰጠው ትኩረት 35 ሺህ መዋዕለ ሕጻናትን መገንባት ተችሏል ብለዋል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ኩረጃን ለማስቀረት፣ ትምህርትን በቴክኖሎጂ ለማስፋፋት እየተደረገ ያለው ሙከራ ተስፋ ሰጪ ነው ሲሉም ገልጸዋል። የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ አበረታች ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛል ሲሉም ተናግረዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትምህርትን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ።
ኢኮኖሚ
በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና በማጎልበት ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል
Jul 7, 2026 23
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና በማጎልበት ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) አባል አገራት የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ላይ ያተኮረ የሁለት ቀናት አውደ ጥናት እየተካሄደ ይገኛል። በአውደ ጥናቱ መክፈቻ ላይ በግብርና ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ ዜና ሀብተወልድ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ለማስፋፋት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል። የመስኖ ስንዴ ልማት፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የአፈር መሸርሸርን መከላከልና ጤንነትን የመጠበቅ፣ የእንስሳት ምርታማነትን የማሻሻያና ሌሎች ስራዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ለማጎልበት የተገኙ ውጤቶች ለኢጋድ አባል ሀገራት ተሞክሮ የሚውሉ መሆናቸውን አመልክተው፤ በቀጣናው የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል የግብርና ልህቀት ማዕከል ለማቋቋም ግብዓት እንደሚሆን አንስተዋል። የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም ስራዎች በአንድ ሀገር ብቻ የሚከናወን ሳይሆን የአገራት ቅንጅት የሚያስፈልግ በመሆኑ ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ጋር የሚከናወኑ ተግባራትን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢጋድ አባል ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ከመቋቋም አኳያ ያሉበት ደረጃ ላይ ያተኮረ ጥናት መካሄዱን ገልጸዋል። በአውደ ጥናቱ ውይይት የሚቀርበው ጥናት የአባል አገራትን የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የልህቀት ማዕከላትን ለማቋቋም፣ ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን የመቋቋም አቅምን ለመገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል። በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) የግብርና እና አካባቢ ጥበቃ ዳይሬክተር ዳሄር ኤልሚ በመወከል የኢጋድ የፖሊሲና የምግብ ዋስትና ኤክስፐርት ሲልቪያ ሄንጋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአየር ንብረት ለውጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አምራች አርሶ አደሮችን እየጎዳ ይገኛል ። የሙቀት መጠን መጨመር፣ ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋዎች፣ የመሬት መራቆት፣ የምግብ ዋስትናና ሌሎች ችግሮች የኢኮኖሚ እድገትን እና ዘላቂ ልማትን እያደናቀፉ ይገኛሉ ብለዋል። በመሆኑም፣ የመቋቋም አቅም ያለው ግብርና፣ ምርታማ እና ዘላቂ የምግብ ሥርዓትን ለመገንባት የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ወሳኝ መሆኑን ነው የገለጹት። በሳይንስ፣ በማስረጃ እና ውጤታማ በሆኑ የእውቀት ሽግግር ላይ የተመሰረቱ ፈጠራ የታከለባቸው እና የተቀናጁ ቀጣናዊ ምላሾችን ይሻሉ ብለዋል። አውደ ጥናቱ የኢጋድ አባል አገራት የምግብ ሥርዓቶች የመቋቋም አቅም ፕሮግራም ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው፤ የቀጣናውን ተጨባጭ ሁኔታዎች በትክክል የሚያንፀባርቅ እና ወደ ተግባር ሊቀየሩ የሚችሉ ምክረ-ሃሳቦች እንዲሁም ቴክኒካዊ እውቀት ለማጎልበት ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው
Jul 7, 2026 28
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ገለጹ። የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) የቀጣናውን የኃይል ንግድ በይፋ ለማስጀመር የሚያስችልና አባል ሀገራትን መግባባት ላይ የሚያደርስ ልዩ ስብሰባ ማካሄድ ጀምሯል። ይህ መድረክ አባል ሀገራትን መግባባት ላይ ለማድረስና የቀጣናውን የኃይል ንግድ በይፋ ለመክፈት ያለመ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣናው አስተማማኝና ዘላቂ አቅርቦት ለመፍጠር የምታደርገውን ጥረት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። ይህ የኃይል ትስስር ለኢትዮጵያ ትልቅ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ባለፈ፣ በአባል ሀገራቱ መካከል በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ዘርፎች ጠንካራ መስተጋብር እንዲፈጠር እያደረገ ይገኛል ብለዋል። በአሁን ወቅት ይህንን ቀጣናዊ መስተጋብር ወደ አንድ የጋራ የአፍሪካ የኃይል ትስስር ለማሳደግ መጠነ-ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) ሊቀመንበር ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፤ የኃይል ትስስሩ ለሀገር በርካታ ጥቅሞች እንዳሉት አብራርተዋል። የኢትዮጵያን ቀጣናዊ ተሰሚነትና የዲፕሎማሲ አቅም ከማሳደግ ባለፈ፤ ከኃይል ሽያጭ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ እያስቻላት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት ከኬንያ፣ ሱዳን፣ ጂቡቲና ታንዛኒያ ጋር ስምምነት በመፍጠር ኃይል እያቀረበች መሆኗን ጠቁመዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም፤ በቀጣይም ከደቡብ ሱዳን እና ከሶማሊያ ጋር የኃይል ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል
Jul 7, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነት ማሳደጉን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው፣ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም፤ መንግሥት የጀመራቸው አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ተከታታይ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ማስቻሉን ገልጸዋል። ግብርና 7 ነጥብ 7 በመቶ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዘንድሮ 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ኩንታል ምርት ተሰብስቧል ብለዋል። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማስፋፋትና ለማዘመን ከተያዙ ቁልፍ ዘርፎች መካከል የኢንዱስትሪው ክፍለ-ኢኮኖሚ ዋነኛውና የትኩረት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል። ከለውጡ በፊት በሀገሪቱ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ በታች የነበረው የማምረት አቅም አሁን ላይ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እፀገነት መንግስቱ እንዳሉት፤ በአምስት ዓመታት የምክር ቤት ዘመን ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እመርታን አስመዝግባለች። በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመትም በብዝኅ ኢኮኖሚ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የተኪ ምርት አቅምን በማሳደግ በወጪ ንግድ ጭምር ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአመራር ቁርጠኝነት፣ የዜጎች ትብብርና የመሪነት ሚናም ኢትዮጵያ ላስመዘገበችው እመርታ ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከቱን አንስተዋል። በምክር ቤቱ የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አራሬ ሞሲሳ በበኩላቸው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ አዋጆች በማፅደቅ ጠንካራ የክትትልና ቁጥጥር የህዝብ ውክልና ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በዚህም ባለፉት ዓመታት በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ፕሮጀክቶች እንዲገነቡ በማስቻልና የከተማ ገፅታን በመቀየር በርካታ ስኬቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። የምክር ቤቱ አባል መስፍን እርካቤ፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ጥያቄና ችግሮች ምላሽ እያገኙ ምርታማነት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት የገጠሟትን የውስጥና የውጭ ፈተናዎች ተቋቁማ በሁሉም ዘርፎች የተሻለ ውጤት አስመዝግባለች ያሉት ደግሞ የምክር ቤቱ አባል የሆኑት አቡኔ አለም ናቸው። የምክር ቤት አባላቶቹ እየተከናወኑ የሚገኙት ውጤታማ የልማት ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ገልጸዋል።
በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ግንባታቸው ተጠናቆ ወደ ሥራ የገቡ የልማት ተቋማት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች የመለሱ ናቸው
Jul 7, 2026 105
ጭሮ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጭሮ ከተማ ግንባታቸው ተጠናቆ ወደ ሥራ የገቡ የልማት ተቋማት የረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄዎችን የመለሱ መሆናቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። በከተማዋ ከ385 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች በዛሬው ዕለት ተመርቀዋል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የተገኙ የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በአገልግሎት አሰጣጥ እና በመንገድ መሠረተ ልማት መስክ የነበሩባቸው ቅሬታዎችና ጥያቄዎች ምላሽ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ አብደላ ኢስማኤል እንዳሉት፤ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ያለመቀናጀትና ኋላቀር አሠራር ለእንግልትና ለተጨማሪ ወጪ ይዳርገን ነበር። አሁን ግን የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በከተማዋ በመጀመሩ አገልግሎቶችን በአጭር ጊዜ እንድናገኝ ስለሚያደርገን ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል። ሌላው ሼህ ኢስማኤል መሐመድ፣ በከተማዋ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ደረጃቸውን የጠበቁ የውስጥ ለውስጥና ዋና መንገዶች እንዲኖሩ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ቀደም ሲል በከተማዋ ምንም የመዝናኛ ስፍራ አልነበረም፤ በአሁኑ ወቅት ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት የመንገድ ዳር መናፈሻ ስፍራዎችና የሳይንስ ካፌ በተለይ ወጣቶች ከአልባሌ ቦታዎች እንዲርቁና በቂ መዝናኛ እንዲያገኙ ያደርጋል ብለዋል። እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያሳድጉና የረጅም ዓመታት የልማት ችግሮችን የፈቱ መሆናቸውን የጠቀሱት ደግሞ አባገዳ አሽም አብደላ ናቸው። ወደ ፊትም ባላቸው አቅም ሁሉ ከልማቱ ጎን በመቆም የሚያደርጉትን ተሳትፎና ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። የጭሮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሐመድ ዑመር እንደገለጹት፤ በዛሬው ዕለት ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት ከ385 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 17 የልማት ፕሮጀክቶች ናቸው። ፕሮጀክቶቹ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ ዳር መዝናኛ ስፍራዎች እና የሳይንስ ካፌን ያካተቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከእነዚህም መካከል ከ100 ሚሊዮን ብር በሚሆን በጀት የተገነባው የአንድ ማዕከል አገልግሎት 68 የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ኢክራም ጠሀ በበኩላቸው፤ በዞኑ የሕብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተገነቡ 24 የልማት ፕሮጀክቶች በዚህ ዓመት ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን አስታውቀዋል። እነዚህ የልማት ፕሮጀክቶች የመንገድ መሠረተ ልማት፣ የውኃ ተቋማት፣ ድልድዮች እና በአርብቶ አደር ወረዳዎች የተገነቡ የውኃ ግድቦችን ያካተቱ መሆናቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በዞኑ የጭሮን ከተማ ጨምሮ በመቻራ፣ ሂርና፣ ገለምሶ እና በዴሳ ከተሞችም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸው፤ ኅብረተሰቡ በአካባቢው እየተገነቡ ባሉ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በክልሉ የመንግስት አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Jul 7, 2026 160
ቡታጅራ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት እንደሚጠናከሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ የቡታጅራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ማህበረሰቡ ሲያነሳቸው የነበሩ ቅሬታዎችን መፍታት የሚያስችሉ አሰራሮችን የማጠናከር ሥራ በትኩረት ይከናወናል፡፡ በዚህም የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቋት በማቅረብ መስጠት የሚያስችለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋፋት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል ብለዋል። የክልሉ መንግስት ከማህበረሰቡ ለሚነሱ የልማት፣ የፍትሀዊ ተጠቃሚነትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን ለማቀላጠፍ የሚያግዙ ማዕከላትን ከማስፋት ባለፈ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሙስጠፋ ሀሰን በበኩላቸው የማዕከሉ ሥራ መጀመር ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን እውን በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ጥረት ያጠናክራል ብለዋል። በማዕከሉ የተለያዩ አገልግሎቶች መሰጠቱም የማህበረሰቡን እንግልት ከማስቀረት በተጨማሪ የተጠያቂነት ስርዓትን በማስፈን ረገድ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ አህመድ እንደገለጹት፣ በከተማው ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ210 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል። ማዕከሉ የመንግስትን አገልግሎት በማዘመን በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት እንደሚያስችልም ተናግረዋል፡፡ በማዕከሉ የስድስት ተቋማት 22 አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንደሚደረጉም ገልጸዋል። በመርሃ ግብሩ የክልሉ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞንና የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠን አካባቢዎችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት የማስገባት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jul 6, 2026 425
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠን የተለያዩ አካባቢዎችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት የማስገባት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ምጣኔ ሀብታዊ እና ልማታዊ ዕድገት እንዲሁም የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025/2030” ስትራቴጂን ቀጣይነት ባለው መንገድ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሐይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታላይዜሽን እንዲሁም ወደ ስማርት ሲቲነት ለመቀየር በከፍተኛ ግስጋሴ ላይ የምትገኝ መሆኗን ገልጸዋል። መንግሥት ለዲጂታላይዜሽን ጉዞ መሠረት የሆኑ ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ ዜጎች ከቴክኖሎጂው ጋር አብረው መራመድ የሚችሉበትን ዕውቀትና ክህሎት እንዲያገኙ በርካታ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ለአብነትም የኢትዮ-ኮደርስ አምስት ሚሊዮን ዜጎች ስልጠና ሰፊ መድረክ መመቻቸቱን ጠቅሰው ለጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች የሚደገፉበት ምቹ መደላድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል፡፡ የተለያዩ ተቋማት የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውን በማስፋት የመንግሥት አገልግሎቶችን፣ የንግድ ሥርዓቶችን እና የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ እንዲያዘምኑ መንገድ መከፈቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት መዘርጋት ሀገሪቱ ወደ ስማርት ከተማነት ለምታደርገው ግስጋሴ ስኬት ወሳኝ በመሆኑ፤ ኢንስቲትዩቱ በትኩረት ሲሠራበት መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ ወደ 40 የሚጠጉ አከባቢዎች ወደ ዲጂታል አድራሻ ሥርዓት ማስገባት የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡ እስከ 2018 ዓ.ም ድረስ በሀገሪቱ የሚገኙ ዘጠኝ ከተሞችን ወደ ዲጂታል አድራሻ ለማስገባት የሚያስችሉ መረጃዎች መሰብሰባቸውን ጠቅሰው፤ ከእነዚህም ውስጥ በተለያዩ ከተሞች የተገነቡ የዲጂታል አድራሻ ሥርዓቶች ቀድመው ወደ አገልግሎት ገብተዋል። የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት መዘርጋቱ ዜጎች በቴክኖሎጂ የተደገፉና ዘመኑን የዋጁ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በመሆኑም የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ይበልጥ ለማፋጠን፣ የተለያዩ አካባቢዎችን ወደዚህ ዘመናዊ አድራሻ ሥርዓት የማስገባቱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡
በክልሉ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን ክህሎት በማሳደግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ አግዟል
Jul 6, 2026 334
ሆሳዕና፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን ክህሎት በማሳደግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ማገዙን የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ሀላፊ ሰላሙ አማዶ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ የ5 ሚሊየን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የቴክኖሎጂ ክህሎትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያስቻለ ነው። ወጣቶቹም በስልጠናው ራሳቸውን በማብቃት ከሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ካሉ ካምፓኒዎች ጋር ተቀናጅተው በመስራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ ገቢያቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን አስረድተዋል። በስልጠናው የብቃት ማረጋገጫ ያገኙ ወጣቶችን ከገበያው ጋር በማስተሳሰር ተጠቃሚ መሆናቸውንም አንስተዋል። በሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው ወደ ሥራ ከተቀላቀሉ ወጣቶች መካከል ጫኪሶ ወልዴ አንዱ ሲሆን በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ያገኘው እውቀት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንደሚያደርገው ተናግሯል። ይህም ከሥራ ጠባቂነት ይልቅ የራሱን ስራ በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ አቅሙን እንሚያጠናክርለት ገልጿል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ለዲጂታል ቴክኖሎጂ የተሰጠው ትኩረት የወጣቶችን ሥራ ፈጣሪነትና ተወዳዳሪነት በማረጋገጡ ሌሎችም የእሱን ተሞክሮ እንዲወስዱ መክሯል። ሌላኛው ወጣት አብይ ላቀው በበኩሉ በኢትዮ ኮደርስ መርሃ ግብር የወሰደው ስልጠና በዘርፉ የነበረውን እውቀት ይበልጥ ለማሳደግ እንዳስቻለው ተናግሯል። ስልጠናው በኦን ላይን ገቢ በማመንጨት ተጠቃሚ መሆን የሚያስችለውን በቂ እውቀት ለማግኘት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረለትም ጠቁሟል። በዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚሰሩ ሥራዎችን በቤቱ ሆኖ በኦን ላይን በመስራት ገቢ ማግኘት መጀመሩን ነው የገለጸው። ባለፉት ሁለት ዓመታት በክልሉ ከ242ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን ተከታትለው የእውቅና የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት፤ ይበልጥ ተደራሽና ቀልጣፋ በመሆን የደንበኞችን እርካታ ያረጋግጣል
Jul 3, 2026 1203
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት፤ የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ተደራሽና ቀልጣፋ በማድረግ የደንበኞችን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ የሚያረጋግጥ መሆኑን የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎችና ባለሙያዎች ገለጹ። አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ተደራሽ እና ጥራት ያለው ለማድረግ የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ ለማኅበረሰቡ ይበልጥ ተደራሽ በመሆን ወደ አገልግሎት የገቡት ሁለት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ ባሶች ቴክኖሎጂዎቻቸው ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት የሰጡ ናቸው፡፡ በዚህም አንደኛው ባስ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ (EV) የሚሠራ ሲሆን ሁለተኛው የተፈጥሮ ጋዝን በመጠቀም የሚንቀሳቀስና አገልግሎት የሚሰጥ ነው፡፡ እነዚህ ተንቀሳቃሽ መስኮቶች የስድስት ቁልፍ የፌዴራል ተቋማትን አገልግሎቶች የሚሰጡ ሲሆን፣ አገልግሎቶቹም ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ በመሄድ የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው፡፡ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተጠቃሚዎች እንደገለጹት፤ ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት እጅግ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገኟቸው ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ አቶ በኃይሉ ወርቁ በሰጡት አስተያየትም ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት ማኅበረሰቡ ባለበት ቦታ ሆኖ ፈጣንና የተቀላጠፈ የመንግሥት አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉን ገልጸዋል። ይህ የዲጂታል ትግበራ አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ ከሙስና የጸዳ፣ ግልጽና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑንም አክለዋል። አቶ አስቻለው ጓዴ በበኩላቸው ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት በየአካባቢው እየተዘዋወረ አገልግሎት መስጠቱ ማኅበረሰቡን ከተጨማሪ ወጪና ከተንዛዛ እንግልት እንደታደጋቸው ገልጸዋል። አሠራሩ ጊዜና ገንዘብን በአግባቡ ለመቆጠብ ያስቻለ በመሆኑም የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል፡፡ በወረፋና በተለያዩ ቦታዎች መጉላላት ሳይኖር፣ በአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን ማግኘት መቻሉ ጊዜንና ጉልበትን በከፍተኛ ደረጃ እየቆጠበላቸው መሆኑን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ወርቅነሽ እሸቱ ናቸው፡፡ የአገልግሎቱ ዲጂታላይዝ መሆን ከተገልጋዩ ባሻገር ለባለሙያዎችም የላቀ የሥራ ተነሳሽነትና ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠሩን አገልግሎቱን የሚሰጡ ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡ የአገልግሎቱ ባለሙያ አቶ አሰግድ ንዋይ እንደገለጹት፣ አዲሱ አሠራር ተቋማትና ባለሙያዎች ወደ ተገልጋዩ ይበልጥ እንዲቀራረቡና ግልጽነት የሰፈነበት አገልግሎት እንዲሰጡ አስችሏል። እሌኒ ውድነህ በበኩሏ፤ አዲሱ የዲጂታል አሠራር ለሠራተኞች ጤናማ የሥራ ድባብ ከመፍጠሩም በላይ፣ የተገልጋዮች እርካታ ለባለሙያው ትልቅ መነሳሳት መሆኑን ጠቁማ፣ ተንቀሳቃሽ መሶብ ማኅበረሰቡን በእጅጉ ማስደሰቱን ገልጻለች። የፌደራል መሶብ አገልግሎት ማዕከል ምክትል ኦፕሬሽናል ዘርፍ ኃላፊ ቤዛዊት ብርሃኔ በበኩላቸው፤ ይህ ዘመናዊ አሠራር ኅብረተሰቡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሁልጊዜም በታላቅ እምነት፣ ምቾትና አስተማማኝ በሆነ መልኩ እንዲያገኝ በር የከፈተ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ስፖርት
ወደ ሩብ ፍጻሜ ለመድረስ የሚደረጉ ተጠባቂ ፍልሚያዎች፦ አርጀንቲና ከግብፅ፤ ስዊዘርላንድ ከኮሎምቢያ
Jul 7, 2026 269
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30 /2018 (ኢዜአ)፦ የ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል። ምሽት አንድ ሰዓት ላይ አርጀንቲና ከግብጽ በአትላንታ ስታዲየም ይጫወታሉ። አርጀንቲና በ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ኬፕቨርዴን 3 ለ 2 አሸንፋለች። የወቅቱ የዓለም ዋንጫ ባለቤት ከተጋጣሚዋ የበረታ ፉክክር ቢገጥማትም፣ ድል ቀንቷት ወደ ቀጣዩ ዙር ተሸጋግራለች። አርጀንቲና በውድድሩ የተሳትፎ ታሪኳ ለ10ኛ ጊዜ ወደ 16ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር አልፋለች። ከዚህ በነበራት የዘጠኝ ጊዜ ተሳትፎ ሰባቱን በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ ስታልፍ በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ተሸንፋለች። ተጋጣሚዋ ግብጽ ከአውስትራሊያ ጋር አንድ አቻ በመለያየት በመለያ ምት የ4 ለ 2 ድል በማስመዝገብ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ 16 ውስጥ ገብታለች። የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር በጥሎ ማለፍ ስታሸንፍ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። አርጀንቲና እና ግብጽ ከዚህ ቀደም በዓለም ዋንጫው ተገናኝተው አያውቁም። እ.አ.አ በ2008 በካይሮ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ባደረጉት የወዳጅነት ጨዋታ አርጀንቲና 2 ለ 0 አሸንፋለች። ሰርጂዮ አጉዌሮ እና ኒኮላስ ቡርዲሶ በወቅቱ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ሰባት ጎሎችን ያስቆጠረው እና በ20 ጎሎች የውድድሩ የምንጊዜም ግብ አስቆጣሪ ሊዮኔል ሜሲ በጨዋታው የሚጠበቅ ተጫዋች ነው። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ሰባት ጎሎችን ያስቆጠረውና በ20 ጎሎች የውድድሩ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ የሆነው ሊዮኔል ሜሲ፣ በጨዋታው ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ተጫዋች ነው። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ሁለት ጎሎችን ያስቆጠረው ኢማም አሹር እና አምበሉ መሐመድ ሳላህ በግብጽ በኩል የሚጠበቁ ተጫዋቾች ናቸው። የጨዋታው አሸናፊ በሩብ ፍጻሜው ከስዊዘርላንድ እና ኮሎምቢያ አሸናፊ ጋር ይገናኛል። ስዊዘርላንድ ከኮሎምቢያ በቢሲ ፕሌስ ቫንኩቨር ስታዲየም ምሽት አምስት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ስዊዘርላንድ አልጄሪያን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ይህም ከ88 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመዘገበችው የጥሎ ማለፍ ድል ነው። ተጋጣሚዋ ኮሎምቢያ ጋናን 1 ለ 0 በመርታት 16 ውስጥ ገብታለች። የደቡብ አሜሪካዋ ሀገር በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ ለአራተኛ ጊዜ በጥሎ ማለፉ ትጫወታለች። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ከዚህ ቀደም አንድ ጊዜ ተገናኝተዋል። አሜሪካ እ.አ.አ በ1994 ባዘጋጀችው 15ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በምድብ አንድ ተገናኝተው ኮሎምቢያ 2 ለ 0 አሸንፋለች። ሄርናን ጋቪሪያ እና ሃሮልድ ሎዛኖ ግቦቹን በወቅቱ ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው። ሀገራቱ ከ32 ዓመታት በኋላ በጥሎ ማለፍ ምዕራፍ ተገናኝተዋል። ቡድኖቹ በአጠቃላይ ሶስት ጊዜ ተገናኝተው ኮሎምቢያ በሁለቱ ድል ሲቀናት በቀሪው አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። የስዊዘርላንድ እና ኮሎምቢያ ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል። የዛሬ ጨዋታ አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው ይገናኛሉ። ሞሮኮ፣ ፈረንሳይ፣ ኖርዌይ፣ እንግሊዝ፣ ስፔን እና ቤልጂየም እስከ አሁን ሩብ ፍጻሜ የገቡ ሀገራት ናቸው።
ቤልጂየም አሜሪካን በመርታት ሩብ ፍጻሜ ገብታለች
Jul 7, 2026 179
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/ 2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ቤልጂየም አሜሪካን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች። ከእኩለ ሌሊት በኋላ በሲያትል ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ቻርልስ ደ ኬቴላሬ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ሃንስ ቫንከን እና ሮሜሎ ሉካኩ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ማሊክ ቲልማን የአሜሪካን ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው ሮሜሎ ሉካኩ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ሶስት አድርሷል። በአጠቃላይ ደግሞ በውድድሩ ላይ ከመረብ ላይ ያሳረፋቸውን ጎሎች ወደ ስምንት ከፍ አድርጓል። ለቤልጂየም ብሔራዊ ቡድንም 93ኛ ግቡን አስቆጥሯል። በጨዋታው ቤልጂየም ከፍተኛ ብልጫ ወስዳለች። የተመለከተው ቀይ ካርድ በአነጋጋሪ ሁኔታ የተነሳለት የአሜሪካው አጥቂ ፍሎሪያን ባሎጉን በጨዋታው ላይ ተሰልፏል። ውጤቱን ተከትሎ ቤልጂየም ወደ ሩብ ፍጻሜ የገባች ሲሆን ለግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ ከስፔን ጋር ትፋለማለች። ከዘንድሮ የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው አሜሪካ የውድድሩ ጉዟዋ 16 ውስጥ ተገቷል። አሜሪካ ከ24 ዓመታት በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜ የመግባት ህልሟ ሳይሳካ ቀርቷል። ጣምራ አዘጋጅ የሆኑት አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በ16ቱ ዙር የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
ስፔን ፖርቹጋልን በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ አለፈች
Jul 7, 2026 263
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/ 2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የ 16ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ተጠባቂ ግብር ስፔን ፖርቹጋልን 1 ለ 0 ረትታለች። ማምሻውን በዳላስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ተቀይሮ የገባው ሚኬል ሜሪኖ በ91ኛው ደቂቃ ግቧን አስቆጥሯል። ፌራን ቶሬስ ኳሱን አመቻችቶ አቀብሏል። ተመጣጣኝ ፉክክር በታየበት ጨዋታ ስፔን የግብ እድሎችን በመፍጠር ተሽላ ተገኝታለች። የ"አይቤሪያ ደርቢ" በስፔን አሸናፊነት ተጠናቋል። ስፔን በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ግብ ያልተቆጠረባት ብቸኛ ሀገር ናት። ውጤቱን ተከትሎ ስፔን ወደ ሩብ ፍጻሜው የገባች አምስተኛ ሀገር ሆናለች። በሩብ ፍጻሜው ከአሜሪካ እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ስፔን የአንድ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ናት። የክርስቲያኖ ሮናልዶዋ ፖርቹጋል የዓለም ዋንጫ ጉዞዋ 16 ውስጥ ተገቷል። የ41 ዓመቱ ሮናልዶ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን የማንሳት ህልሙ ሳይሳካ ቀርቷል። ተጫዋቹ ዘንድሮ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ መሆኑን ከጨዋታው በፊት ገልጾ ነበር። ሁለቱ ሀገራት ዓለም ዋንጫን ያሸንፋሉ ተብለው ግምት የተሰጣቸው ናቸው። አሜሪካ ከቤልጂየም ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በሲያትል ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ፖርቹጋል ከስፔን : ተጠባቂው የጥሎ ማለፍ ፍልሚያ
Jul 6, 2026 607
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፡- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ የሚገቡ ሀገራት የሚለዩባቸው ሁለት ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ። ምሽት አራት ሰዓት ፖርቹጋል ከስፔን በዳላስ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል። ፖርቹጋል በ32ቱ የጥሎ ማለፍ ዙር ክሮሺያን 2 ለ 1 ስታሸንፍ ስፔን በበኩሏ ኦስትሪያን በመርታት ቀጣዩን ዙር ተቀላቅላለች። የአውሮፓ እግር ኳስ ኃያላኑ በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2010 ባዘጋጀችው 19ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በተመሳሳይ 16 ውስጥ ተገናኝተው ስፔን በዴቪድ ቪያ ጎል 1 ለ 0 ማሸነፏ ይታወሳል። በወቅቱ ስፔን የዓለም ዋንጫው ባለቤት መሆን የቻለች ሲሆን፣ ይህ ስኬትም እስካሁን ድረስ በታሪኳ ያስመዘገበችው ብቸኛ የዓለም ዋንጫ ድሏ ነው። በሩሲያ እ.አ.አ በ2018 በተካሄደው 21ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በምድብ ሁለት ተገናኝተው ሶስት አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ሲሆን በወቅቱ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለፖርቹጋል ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ብሔራዊ ቡድኖቹ ከዚህ ቀደም እርስ በእርስ ባደረጓቸው 41 ጨዋታዎች ስፔን 17 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ስትይዝ ፖርቹጋል ብስድስቱ ድል ሲቀናት በቀሪ 18 ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። በዛሬው ጨዋታ የ41 ዓመቱ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና የ18 ዓመቱ ላሚን ያማል የሚጠበቁ ሲሆን በጨዋታው ተመጣጣኝ እና አዝናኝ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ በሩብ ፍጻሜው ከአሜሪካ እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ይገናኛል። አሜሪካ ከቤልጂየም ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት በሲያትል ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ከዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው አሜሪካ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ቦሲኒያ ሄርዞጎቪናን 2 ለ 0 ማሸነፏ እንዲሁም ተጋጣሚዋ ቤልጂየም በበኩሏ ሴኔጋልን ከ2 ለ 0 መመራት ተነስታ ውጤቱን ቀልብሳ 3 ለ 2 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር መቀላቀሏ ይታወቃል። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም በዓለም ዋንጫው ሁለት ጊዜ ተገናኝተዋል። ኡራጓይ እ.አ.አ በ1930 ባዘጋጀችው የመጀመሪያ የፊፋ የዓለም ዋንጫ በምድብ አራት ተገናኝተው አሜሪካ 3 ለ 0 አሸንፋለች። በርት ፓቴናውድ ሶስቱንን ግቦች ከመረብ በማሳረፍ በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ሀትሪክ የሰራ ተጫዋች መሆንም ችሏል። ብራዚል እ.አ.አ በ2014 ባዘጋጀችው 20ኛው ፊፋ ዓለም ዋንጫ 16 ውስጥ ተገናኝተው ቤልጂየም 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ አልፋለች። ኬቨን ደ ብሮይን እና ሮሜሎ ሉካኩ ግቦቹን ሲያስቆጥሩ ሁለቱም ተጫዋቾች በአሁኑ የዓለም ዋንጫ የቤልጂየም ስብስብ ውስጥ ይገኛሉ። ጁሊያን ግሪን በወቅቱ የአሜሪካን ብቸኛ ጎል ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ሁለቱ ሀገራት ከ12 ዓመታት በኋላ በድጋሚ 16 ውስጥ ተገናኝተዋል። በአጠቃላይ ሀገራቱ እርስ በእርሳቸው ሰባት ጊዜ ተጫውተው ቤልጂየም ስድስቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ስትይዝ በቀሪው አንድ ጨዋታ (በመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ) አሜሪካ ድል ቀንቷታል። በአሜሪካ በኩል በውድድሩ ሶስት ግቦችን ያስቆጠረው የአሜሪካው ፍሎሪያን ባሎጉን ከቦሲኒያ ጋር በነበረው ጨዋታ የተመለከተው ቀይ ካርድ አግባብ ባለመሆኑ ምክንያት ተነስቶለት በጨዋታው ላይ እንዲጫወት መወሰኑን ፊፋ አስታውቋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋኒቲኖ የቀይ ካርድ ውሳኔው በድጋሚ እንዲታይ ደውለው መጠየቃቸውን ተከትሎ ቀይ ካርዱ መነሳቱ የዓለም አቀፉ እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል ላይ የተአማኒነት ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል። ተጋጣሚዋ ቤልጂየም ውሳኔውን ፍጹም ተቀባይነት የለውም ስትል የተቃወመች ሲሆን የሁሉም ተሳታፊ ሀገራት መብት እንዲጠበቅና በእግር ኳሱ ፍትሃዊነት እንዲሰፍን ሁሉንም አማራጮች እንደምትመለከት አስታውቃለች። ትራምፕ ውሳኔውን ተከትሎ ፊፋን ያመሰገኑ ሲሆን ፍትሃዊነትን ያሰፈነ ውሳኔ ሲሉ መግለጻቸውን ተከትሎ ውሳኔው ከጨዋታው በፊት ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል። ለቤልጂየም በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በዓለም ዋንጫው ያስቆጠሩት ሊአንድሮ ትሮሳርድ እና ሮሜሎ ሉካኩ በጨዋታው የሚጠበቁ ተጫዋቾች ናቸው። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ጨዋታው አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው ይገናኛሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ አሻራ እያስገኘ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል
Jul 7, 2026 113
ጎንደር፤ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ):- የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር እያስገኝ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማስቀጠል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኜው ገለጹ። ከተማ አስተዳደሩ የክረምት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዘዞ ክፍለ ከተማ በአባ ሳሙኤል ፓርክ ዛሬ አስጀምሯል። ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ቻላቸው ዳኜው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር ባጭር ጊዜ ውስጥ ዘርፈ ብዙ እና ተጨባጭ ለውጥ ለማስመዝገብ ያስቻለ ነው። በመርሃ- ግብሩ የለሙ ተፋሰሶች አርሶ አደሩ በመስኖ፣ በእንስሳት እርባታና ማድለብ፣ በንብ ማነብ ፣ በመኖና ሌሎች የልማት ዘርፎች በመሳተፍ ተጠቃሚ መሆን የቻለበት ነው ሲሉ ገልፀዋል። በተለይም በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት አርሶ አደሩ ዘላቂና ተጨማሪ ሃብት እንዲያፈራ መርሃ ግብሩ ሰፊ እድል ለመፍጠር እያስቻለ መሆኑንም ነው ያነሱት። በመሆኑም በዘንድሮው ዓመትም የአትክልት ፍራፍሬና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ላይ በማተኮር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እንደሚካሔድ አስረድተዋል። የከተማ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አበራ አደባ ፤በበኩላቸው በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ476 ነጥብ 5 ሔክታር መሬት ላይ 4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞች እንደሚተከሉ ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በተካሄደው መርሃ ግብርም 758 ሺህ ዜጎችን በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። በዘንድሮ ዓመትም ባለፉት ዓመታት የተገኘውን ተጠቃሚነት ለማስፋትም 500 ሺህ የአቡካዶ፣ ሙዝ፣ ማንጎና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን አስገንዝበዋል። የተተከሉ ችግኞችን የመጽደቅ ምጣኔ 95 በመቶ ለማድረስ ማህበረሰቡን ያሳተፈ የእንክብካቤና ጥበቃ ስራ እንደሚከናወን አስገንዝበዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለእንስሳት መኖ፣ ለንብ ማነብ፣ ለከብት ማድለብና በወተት ልማት ዘርፍ እድገት ማስመዝገብን ጨምሮ ስርአተ ምግብም እንዲሻሻል ማድረጉን አስረድተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ
Jul 6, 2026 677
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፡-የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከ30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ(ኮፕ 30) ፕሬዝዳንት አምባሳደር አንድሬ አራንሃ ኮሪያ ዶ ላጎ እና ከቡድናቸው ጋር ውይይት አድርገዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) አስተናጋጅ ለመሆን በምታደርገው ዝግጅት ላይ፣ ከቀደምት አዘጋጅ ሀገራት ልምድ መቅሰም ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ሆኗል። በዚህም መንፈስ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዝዳንት አምባሳደር አንድሬ አራንሃ ኮሪያ ዶ ላጎ እና ከቡድናቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የውይይቱ ዓላማ ዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ጉባኤ ከማዘጋጀት ጋር የተያያዙ ዕውቀቶችን እና የተወሰዱ ትምህርቶችን መለዋወጥ መሆኑን ተመላክቷል።
በአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን ጠንካራ የዕፅዋት ጤና ጥበቃ ሥርዓት መገንባት ይገባል
Jul 6, 2026 387
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ አህጉር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ውጤታማ የዕፅዋት ጤና ጥበቃ ሥርዓት መገንባት ወሳኝ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። "የእፅዋት ሀብቶችን እና ተቋማትን ለመጠበቅ የአፍሪካ ሀገራትን በሳይንስ እና በዲጂታል መሳሪያዎች ማብቃት" በሚል መሪ ኃሳብ የተዘጋጀው የአፍሪካ ዕፅዋት ጤና ጥበቃ ፕሮግራም የስትራቴጂክ አጋርነት መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ አፍሪካ ግብርናውን ለመለወጥና ዘላቂ ልማት ለማምጣት የምታደርገው ጥረት በድንበር ተሻጋሪ ተባዮች፣ በወራሪ ዝርያዎች፣ በድንገተኛ በሽታዎች እና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ከፍተኛ አደጋ ተደቅኖበታል። እነዚህ ተግዳሮቶች በምርት፣ በብዝሃ ሕይወት እና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ በመሆናቸው፣ በእፅዋት ጤና ላይ መዋዕለ ነዋይ ማፍሰስ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ስኬት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ተባይና የእፅዋት በሽታዎች በድንበር የማይገደቡ በመሆናቸው፣ የትኛዋም ሀገር ተግዳሮቶቹን ብቻዋን መፍታት ስለማይቻል አህጉራዊ የጋራ ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል። ጠንካራ የዕፅዋት ጤና ጥበቃ ሥርዓት መገንባት የግብርና ኢንቨስትመንቶችን ለመጠበቅ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እና የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳርን ለመንከባከብ መሠረታዊ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ደህንነቱ የተጠበቀና ተወዳዳሪ የንግድ ሥርዓትን ለማመቻቸት እንዲሁም የምግብ ሥርዓትን የመቋቋም አቅም ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። በኢትዮጵያም ዘላቂ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማምጣት የዕፅዋትን ጤና የመጠበቅ ተግባር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል። የዓለም አቀፉ የዕፅዋት ጥበቃ ኮንቬንሽን ጸሃፊ ኤንሪኮ ፔሮቲ በበኩላቸው ድርጅቱ ጠንካራ እና የበለጠ የመቋቋም አቅም ያለው የዕፅዋት ጤናን ለመገንባትና የምግብ ዋስትናን ለመደገፍ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ገልጸዋል። አጋርነቶችን ማጠናከርና አዳዲሶችን መፍጠር እንደሚገባ ገልጸው፣ በአፍሪካ የዕፅዋት ጤና ፕሮግራም በኩል የተመዘገበው አስደናቂ እድገት በዓለም አቀፍ ደረጃ የላቀ ተፅዕኖ ለመፍጠር መሠረት መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኢንተር-አፍሪካን የዕፅዋት ጤና ጥበቃ ምክር ቤት አስተባባሪ ሳሊው ኒያሲ (ዶ/ር)፤ ተቋማቸው ለብሔራዊ ተቋማት የክትትል፣ የላቦራቶሪ ምርመራና የመከላከል አቅምን በማሳደግ፤ በሳይንስ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ አሰጣጥንና ቀጣናዊ የመረጃ ልውውጥን እያጠናከረ ይገኛል ብለዋል። ይህ ፕሮግራም የአፍሪካ ህብረትን የዕፅዋት ጤና ስትራቴጂ ትግበራ የሚደግፍ እና በአካታች የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮግራም ስር የተገለጹትን የአጀንዳ እ.አ.አ 2063 ለማሳካት እየተሰሩ ካሉት ስራዎች አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት ጊዜያዊ ተወካይ ኦርላንዶ ሶሳ በበኩላቸው፣ ለስኬቱ የመንግስታት፣ የቀጣናዊ ድርጅቶች፣ የልማት አጋሮች፣ የቴክኒክ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ የተቀናጀ አጋርነት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የገንዘብ ድጋፍ፣ የቴክኒክ እውቀት፣ ስልጠና፣ የምርመራ አገልግሎት፣ የዲጂታል ድጋፍ ጋር የተያያዙ አስተዋፅኦዎች ተቀናጅተው ዘላቂ አቅምን ለመገንባት መዋል እንዳለባቸው ተናግረዋል። ለአርሶ አደሮች እና በዕሴት ሰንሰለቱ ውስጥ ላሉ ተዋናዮች ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያን ስም ከፍ ያደረገ ነው
Jul 6, 2026 357
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ ዐሻራ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያን ስም ከፍ ያደረገ መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራርና ሠራተኞች በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ጎተራ ማሳለጫ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ አከናውነዋል። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሁሉም መስክ ተጨባጭ ሀገራዊ ለውጦች እንዲመዘገቡ መሰረት እየጣለ ነው። የተሸረሸሩ እና የተጎዱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ አስችሏል ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፤ በምግብ ራስን የመቻል ግቦችን በማሳካት ረገድ አዎንታዊ ውጤቶች እየተመዘገበበት ነው ብለዋል። አገልግሎቱ ባለፉት ዓመታት በመርሃ ግብሩ በንቃት መሳተፉን ጠቅሰው፤ በ2018 በጀት ዓመት በአረንጓዴ አሻራ እና በተለያዩ በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያጎሉ ተግባራትን በሰፊው እንደሚያከናውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የወሰደችው የአረንጓዴ ዐሻራ ተግባራዊ ምላሽ ስሟን በዓለም መድረክ ከፍ ማድረጉን አስረድተዋል። ከዚህም ባለፈ ስለ አፍሪካ የሚነሱ የተዛቡ ትርክቶችን በማስተካከል ከፍያለ አህጉራዊ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በአዲስ አበባ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ብርሃኑ አበራ በበኩላቸው፤ አረንጓዴ ዐሻራ የደን ሽፋን እንዲጭምር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። ሁሉም በየአካቢው ችግኞችን በመትከል ሀገራዊ ኃላፊነቱን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የፕላንኒንግ ዳይሬክተር መሳይ አበበ እንደገለጹት፤ ዛሬ የምንተክለው ችግኝ ለቀጣዩ ትውልድ ዋስትና ነው ያሉ ሲሆን፤ ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክቦ ለውጤት ማብቃት ከኛ ይጠበቃል ብለዋል። አሻራዬን በማኖሬ እኮራለሁ ያሉት የአገልግሎቱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር ማስተዋል ገዳ፤ የምንተክለው ችግኝ ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ ተስፋን ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል። በቀጣይም የአረንጓዴ ዐሻራ ዘላቂ ግቦች እንዲሳኩ የሚጠበቅብኝን እወጣለሁ ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 16894
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 11185
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 9985
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 9884
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jul 5, 2026 779
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018(ኢዜአ):- የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? ኢትዮጵያ እያከናወነች ነው የገጠር ትራንስፎርሜሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት የተጀመረው የከተሞች ኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩም ተስፋፍቶ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗርና አመጋገብ እንዲሁም ጤናን መሰረት በማድረግ የገጠር ኮሪደር ልማት በመከናወን ላይ ይገኛል። ለጤናም ይሁን ለኑሮ ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ለዘመናት በተመሳሳይ ሁኔታ የኖረው አርሶና አርብቶ አደሩ አሁን ላይ መሰረታዊ የአኗኗር ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በገጠር የኮሪደር ልማት የሰዎችና እንስሳት መኖሪያ እየተለየ፤ በባዮ ጋዝ እና በፀሃይ ብርሃን በሚሰራ የሃይል ምንጭ መብራት ማግኘትና ምግብ መስራት የተቻለበት፤ በጓሮ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎችን መመገብ የሚቻልበት ዘመናዊ አኗኗር ጀምረዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን የልማት እንቅስቃሴው በጅምር ላይ ቢሆንም በብዙ አካባቢዎች እየተስፋፋ ሞደል መንደሮች እየተበራከቱ መጥተዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ሀማሳ በ79 ነጥብ 4 ሄክታር መሬት ላይ የተሰራው ሞዴል መንደር የዚሁ ጥረት ማሳያ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቆ ለነዋሪዎች የተላለፈው የሀማሳ ሞዴል መንደር በአንድ ግቢ ውስጥ የንጽህና መጠበቂያ፣ የተደራጀ የቤት እንስሳት ማቆያ፣ በባዮ ጋዝ የሚሰራ የሃይል አቅርቦትን እንዲሁም የተሟላ የጓሮ ግብርናን ማእከል አድርጎ የተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም መንግሥት በተለያዩ የገጠር አካባቢዎች ሞዴል ቤቶችን መስራቱን አስታውሰው ከዚህ በመነሳት ነዋሪዎቹ በራሳቸው ተነሳሽነት የራሳቸውን መኖሪያዎች መገንባት ጀምረዋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው ''ንጽህና ካለ ጤና አለ፤ ምግብ ካለ ጤና አለ፤ የተስተካከለ ኮሪደር ካለ ሰላም አለ። እነዚህ ጉዳዮች ከፍተኛ ግምት ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል። የዜጎቻችንን ሕይወት ይቀይራሉ፤ የአኗኗር ዘዬአችንን ያሻሽላሉ፤ ኢትዮጵያን ወደ ምናስበው ከፍታ ወደ ምናስበው መሻሻል የመውሰድ አቅም አላቸው'' ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ቀጥሎ በጋሞ ዞን የ'ዮ ሆልዲንግ’ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከጥቂት ዓመታት በፊት ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚሆን የድንጋይ ከሰል ከውጭ ሀገር ለማስገባት እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር ውጪ የሚደረግ መሆኑን አንስተዋል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ የተለያዩ የከሰል ማምረቻ ፋብሪካዎች ተመርቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውንና ይህም የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ ለውጭ ገበያ የማቅረብ እድል ይፈጥራል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአርባምንጭ ዘመናዊ የኮንፈረንስ ሪዞርት መርቀው ስራ ያስጀመሩ ሲሆን በዶርዜ ሎጅ እና አካባቢው መሰረተ ልማቶችን እንዲሁም የአርባ ምንጭ ከተማን የኮሪደር ልማት፤ በከተማዋ የሚገኘውን ኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓንም ጎብኝተዋል። በሁሉም ዘርፎች ኢትዮጵያ ማከናወኗን አጠናክራ ቀጥላለች፤ እድገትና ማንሰራራቷ ላይቀለበስ ጉዞውን ቀጥሏል። ከዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች አንዱ የቱሪዝም ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት እንዳስታወቀው የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በዓለማችን ከፍተኛ ተጓዦች ከተመረጡ የዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች መካከል አንዱ ሆኗል። በዩሮኒውስ የዜና አውታር በተደረገ ጥናት፤ ሁሉንም የዓለም ክፍሎች ያዩ አንጋፋ ተጓዦች ካስቀመጧቸው ተወዳጅ የዩኔስኮ የዓለም ቅርሶች መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በግንባር ቀደምትነት ተቀምጧል። በዚሁ ሳምንትም ከአርባ በላይ ሀገራት እና ከአሥር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ዲፕሎማቶች የላሊበላ ከተማና ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። ይህ ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑክ በቆይታው ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን፣ የሕንጻ ጥበብ እና የኢንጂነሪንግ ጥበብ ማስተርፒስ እንዲሁም የሃይማኖትና የታሪክ ሕያው ምስክር የሆኑትን የዓለም ቅርስ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አስተማማኝ መከታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ያሰለጠናቸውን ተመራቂዎች በዚሁ ሳምንት አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ሰራዊቱ የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝ መልኩ እየጠበቀ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ ታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች ግንባር ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያን ከባሕር ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ “ፅምዶ” በሚል የተሰለፉ አካላት ስለመኖራቸው ተናግረዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአደረጃጀት ልዩ እና በዘመናዊ ትጥቅ ተጠናክሮ በማንኛውም ሁኔታ ለሀገሩ ክብርና ሉአላዊነት መጠበቅ አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል። የ12ኛ ክፍል ፈተና በሳምንቱ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ስኬታማ በሆነ መልኩ ተከናውኗል። በሁሉም አካባቢዎች ተፈታኞች በበይነመረብ (ኦንላይን) እንዲሁም በወረቀት እንደየ ዝግጅቱና ምቹ ሁኔታውን መሰረት በማድረግ ፈተናውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በገጠር ኮሪደር አዲስ የህይወት ምእራፍ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የጊምቦ ወረዳ በተገነባው ሞዴል የገጠር መንደር የሚኖሩ አርሶ አደሮች አዲስ የህይወት ምእራፍ መጀመራቸውን ገልጸዋል። የኤሌክትሪክና ሌሎች አገልግሎቶች የተሟላለት የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር የአኗኗር ዘይቤያችንን ምቹና ዘመናዊ አድርጎታል ያሉት ነዋሪዎቹ ይህንን ላደረጉ ሁሉ እናመሰግናለን ብለዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ የተገነባውን የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የግብርናና ገጠር ሽግግርን እውን በማድረግ የአርሶ አደሩን አኗኗር ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ገልፀው የመብራት፣ የውሃ፣ የመንገድን ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን አርሶ አደሩ በአቅራቢያው ማግኘት የሚያስችልና የኢኮኖሚ አቅሙን የሚያሳድጉ መሆናቸውን በወቅቱ ተናግረዋል። በቀጣይም ተግባሩን በማስፋት ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግን ፍልሰት ለማስቀረት በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ አኔ ዲማ ወረዳ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰኣዳ አብዱረህማንና የከተማው ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎችም የአከባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰዓዳ አብዱረህማን በወቅቱ፤ ዛሬ የምንተክላቸው ችግኞች ለሀገራችን ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ የሚሰጡ ናቸው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለትውልድ ቀጣይነት አስተማማኝ ዋስትና ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)፤ በሸገር ከተማ የአካባቢውን አረንጓዴነት ለማረጋገጥና ኢኮኖሚውን ለመደገፍ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን የተለያዩ ዝርያ ያላቸውና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር ገብተናልም ብለዋል። የባቡር መስመር ጥገና የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በቅርቡ የጥገና ስራው የተጀመረውን የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ የባቡር መስመር ፕሮጀክት የጥገና ሂደት በዚሁ ሳምንት ጎብኝተዋል። ከአዋሽ -ኮምቦልቻ -ሃራ ገበያ 392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን ፕሮጀክት በአራት አቅጣጫ የጥገና ሥራው እየተከናወነ መሆኑም ታውቋል። ለልማት ተነሽዎች የተገነቡ ቤቶች በዚሁ ሳምንት የጅማ ከተማ አስተዳደር ለልማት ተነሺዎች ያስገነባውን 300 መኖሪያ ቤቶች መርቆ ማስረከቡን እንመለከታለን። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ፤ በክልሉ በገጠርም ይሁን በከተሞች ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሃ ቀመር፤ በከተማው በርካታ ፕሮጀክቶች በመንግስት እየተከናወኑ እንደሆኑና የተጠናቀቁትም ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በከተማዋ በዚህ አመት 80 የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ጠቅሰው ዛሬ ለልማት ተነሺዎች ተገንብተው የተላለፉ መኖሪያ ቤቶች የዚሁ ጥረት አንድ አካል ናቸው ብለዋል። እነዚህ መኖሪያ ቤቶች ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው ግንባታቸው ተጠናቆ ለ300 አባወራና እማወራዎች ተላልፈዋል ብለዋል።
ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች
Jun 29, 2026 3507
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • ምንድንነት የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም ‘አስም’ እንደሚባልም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የኪንታሮት ህመም እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? • ምልክቶች የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ጠቁመዋል። ምልክቶቹም በአብዛኛው በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ አስገንዝበዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር)፣ የእንስሳት አይነ ምድር ሽታዎች ለዚህኛው አስም አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን አስረድተዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑንም ተናግረዋል። • አጋላጭ (ለህመሙ መባባስ) መንስዔዎች አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የዓየር ብክለት፣ ጭስ)፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ዓይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? 👉ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎችዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ 👉 በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ 👉 በቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ ሙቀት የሚሰጡ መከላከያ ልብሶችን መልበስ፤ 👉 ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ • ሕክምናው የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የዓየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ከ 3 እስከ 10 በመቶ ያህሉ የዓለም ሕዝብ በአስም ተጠቂ መሆኑንም ጠቁመዋል። #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢዜአ #የጤና_ነገር
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 3234
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ከተጽዕኖ ፈጣሪነትና ተደማጭነት መጎልበት እስከ የአኅጉር ድምጽ መሆን - የኢትዮጵያን ታላቅነት የገለጠው የዲፕሎማሲው ዘርፍ ስኬት
Jun 25, 2026 3929
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቷ የፓን አፍካኒዝም ንቅናቄን በማንሳት አኅጉራዊ ተቋማት እንዲመሠረቱ ፊታውራሪ ከመሆን ጀምሮ ለጎረቤቶቿ ሰላም ጉልኅ ሚና ተጫውታለች፤ አሁንም ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔን እያሰረጸች በርካቶች እንዲጋሯት አድርጋለች። እንደ ሀገር ከለውጡ መንግሥት ወዲህ ከተገኙ በርካታ ትላልቅ ስኬቶች መካከል በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው አንዱ ነው። ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የለውጡ መንግሥት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ዋነኛ መለኪያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ነው። የኢትዮጵያ ሁኔታዎችን የማሰብ፣ የመፈለግና የመከወን ሂደት ንጥል (ለራስ ብቻ የሚል) ሳይሆን፤ በወንድማማችነት/እህትማማችነት ዕሳቤ በጋራ ማደግን ያነገበ ነው። ይህ ሂደቷም በበርካታ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ እንዲሁም አኅጉር አቀፍ ተቋማት ተወድሷል። በዚህም ሐሳቦቿ ቅቡል ሲሆኑ ተመልክተናል። ኢትዮጵያ የ#BRICS አባል መሆን መቻሏ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ይህም ተሰሚነቷን ያረጋገጠ ማስረጃ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ተያያዥ ጉዳዮች ዘርፈ-ብዙ ጥቅም በማስገኘት የበለጸገች ኢትየጵያን ዕውን የማድረግ ጉዞው ያፋጥናል። ወዲህ ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልና አፍሪካን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና መመረጧም የአኅጉሪቱ ድምጽ መሆኗን ይነግረናል። ዓለም አቀፍ ብሎም አኅጉር አቀፍ የሆኑ በርካታ ኮንፈረንሶችም በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እንዲካሄዱ መደረጉ አንድምታው ብዙ ነው። በብቃት ማስተናገዷ ደግሞ ሌላኛው ጥንካሬዋ። ሌላው የሀገራችንን የተጨበጠ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት የሚገልጽልን፤ የዓለም የዓየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን (COP32) እንድታዘጋጅ መመረጧ ነው። ይህን ትልቅ ዕድል በርካቶች ስለተመኙት አላገኙትም፤ ኢትዮጵያ ግን ዜጎቿን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባከናወነችው ያላሰለሰ ትጋት አግኝታዋለች። ግጭት ባለባቸው የቀጣናው ሀገራትም በመንግሥታቱ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት ሥር ከምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባለፈ፤ በግሏ የሰራችው ብዙ ነው። ከራሷ አልፋ ለጎረቤቶቿ ዘብ መሆኗ፤ በአብሮነት መኖርን እና በጋራ ማደግን በተግባር የገለጠች ሀገርም ያደርጋታል። ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ በሚለው ቅድሚያ ለሀገር በቀል ዕውቀቶች በሩን ክፍት ባደረገው ትጋቷም፤ በበርካታ የአኅጉሪቱ ሀገራት ዘንድ ምሥጋና አስችሯታል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲዋም በተለያዩ ሀገራት በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎቿን ከሀገራቱ እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመነጋገር በተሳካ ሁኔታ ልጆቿን ወደ ዕቅፏ መልሳለች፤ በቅርቡ በሳዑዲ ዓረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምኅረት ዐዋጅ እንዲሰጣቸው መደረጉ አንድ ማሳያ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን ጨምሮ በተለያዩ አኅጉራት በሚገኙ ሀገራት መሪዎችና ተወካዮች ዘንድ በስፋት የተመረጠችና የተጎበኘች ሀገር መሆኗን ማስታወስ ተገቢ ነው። ከጉብኝት ባለፈ ትላልቅ ስምምነቶችም የተፈራረመች መሆኗን ልብ ማለት ይገባል፤ ይህም የምታነሳውን ሐሳብ ገዥነትና የአፍሪካ መግቢያ በር መሆኗን ያሳያል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ መሆኑን መረዳት ይገባል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድርድር ሂደት የተጎናጸፈችው የዲፕሎማሲ ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መነቃቃት መፍጠሩንም ማጤን ያስፈልጋል። ይህ የተሳካው ሀገሪቱ ኢትዮጵያ መንገዷም የጋራ ልማትን የሰነቀ ዕውነት በመሆኑ ነው። በቀጣይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለአንዲት ሀገራቸው አምባሳደር በመሆን፤ የዲፕሎማሲውን ሥራ በይበልጥ ማገዝ ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ካልሠሩ ማን ለሀገራቸው ሊሠራ ይችላል?
ትንታኔዎች
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 1426
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 1748
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 1817
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 5533
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 7698
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 19202
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 12260
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 18013
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 3912
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 2982
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።