ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቀቂ አዋጅ ኢትዮጵያ ያላትን የዕጽዋት ሀብት ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመንከባከብ አቅም ይፈጥራል
Oct 22, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቀቂ አዋጅ መዘጋጀት ኢትዮጵያ ያላትን የዕጽዋት ሀብት ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመንከባከብ አቅም እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ ገለጹ፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በዕጽዋት ጥበቃ እና ኳራንቲን ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት የአስረጂ መድረክ አካሂዷል። የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዕጽዋት ሀብት የታደለች የበርካታ ብዝሀ ህይወት መገኛ ብትሆንም የተፈጥሮ ሀብቷን በአግባቡ መጠቀም የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ የላትም፡፡ ከዚህ በፊት የነበረው ህግ የግብርናን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንቅፋት የሆነውን መጤና ወራሪ ተባይ ለመከላከል ውስንነት ነበረበት ብለዋል፡፡ በተለይም በዕጽዋት ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ ተባዮችን አስቀድሞ መከላከልና ጠንካራ የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት አያስችልም ነበር ነው ያሉት፡፡ በዚህም የዓለም አቀፍ የዕጽዋት ጥበቃ ስምምነትን መነሻ ያደረገ የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ የዕጽዋት ሀብቶቿ ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያገኙ እና መጤና ወራሪ ተባዮችን መከላከል የሚያስችል አቅም ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ይሄውም ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ ያላትን ተሳትፎ በማሳደግ ከዕጽዋት ዘርፍ የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንድታገኝ እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር)፤ መንግስት የግብርናን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቀቂ አዋጅ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ገልጸው፤ ተባይ በዕጽዋት ላይ የሚያደርሰውን የምርት ብክነት መቀነስና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ያስችላል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወንዳለ ሀብታሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ በዓለም አቀፍ ገበያ መወዳደር የሚያችሉ መስፈርቶችን የያዘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት በአግባቡ ጥቅም ለማዋል ወሳኝ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ የግብርና ኤክስቴንሽንን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል ነው
Oct 22, 2025 49
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ይፋዊ የባለድርሻ አካላት ውይይት አካሂዷል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የተዘጋጀው ከኢትዮጵያ የግብርና ዕድገት ጋር የሚራመድ የግብርና ኤክስቴንሽን ህግ በማስፈለጉ ነው፡፡ በረቂቅ አዋጁ ላይ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የረጅም ጊዜ ውይይትና ጥናት መደረጉን ገልጸው፤ በዚህም ከዘርፉ ተዋንያን ገንቢ አስተያየቶች ተሰጥተዋል፤ በግብዓትነትም ተካተዋል ብለዋል፡፡ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር) መንግስት የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን የሚፈለገውን ዕድገት ለማስመዝገብ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ በዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ እና አስተዳደር ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ያስችላል ብለዋል፡፡ በግብርና ኤክስቴንሽን ዘርፍ በመንግስት ብቻ ሲከናወኑ የነበሩ ተግባራት ላይ ሌሎችም የዘርፉ ተዋንያን እንዲሳተፉ የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፤ ዘርፉ ራሱን በቻለ ህግ እንዲመራ የሚያደርግ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ የግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወንዳለ ሀብታሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ የአርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ፍላጎት መነሻ በማድረግ ተሞክሮዎችን በሚያሰፋ መልኩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ልምድና እውቀት የያዘ መሆኑን ገልጸው፤ የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የጎላ አበርክቶ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
በአማራ ክልል የፍትህ አስተዳደር ሥርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 22, 2025 45
ባህር ዳር፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የፍትህ አስተዳደር ሥርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ። የፍትህ ቢሮውና የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በቅንጅት መስራት በሚያስችላቸው ተግባራት ላይ ያተኮረ የጋራ የትብብር ማዕቀፍ ሰነድ ዛሬ ተፈራርመዋል። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ብርሃኑ ጎሽም በመርሃ ግብሩ እንደገለጹት ወንጀሎችን ቀድሞ ለመከላከልና የፍትህ ስርዓቱን ለማዘመን በትኩረት እየተሰራ ነው። የፍትህ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ህብረተሰቡን በፍትሃዊነት ለማገልገል በቅንጅትና በትብበር መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል። ይህም በክልሉ ሰላም፣ ልማትና የህግ የበላይነትን በአስተማማኝ ሁኔታ በማረጋገጥ ጠንካራ የፍትህ ስርዓት በየደረጃው ለመገንባት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። የፍትህ ቢሮው እና የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ወንጀልን በመከላከል፣ ምርመራና ክስን በጥራትና በውጤታማነት በማከናወንና ሌሎች ስራዎችን በጋራ በመስራት ቅቡልነትን ማረጋገጥ ይገባል ነው ያሉት። ይህም የሃብት ብክነትን በመቀነስ፣ ጉልበትና ጊዜን በመቆጠብ ስኬትን በጋራ ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ገልጸው ዛሬ የተደረገው ስምምነትም ይህን የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት አገልግሎትን ለማጠናከር የፍትህና የፖሊስ ተቋማት በጋራ ተናበው መስራት አስፈላጊ ነው። የፖሊስና የፍትህ ተቋማት ተግባር የማይነጣጠሉ ናቸው ያሉት ኮሚሽነሩ ተቋማቱ ተቀናጅተውና ተናበው በመስራት የፍትህ አስተዳደር ስርዓቱን ማጠናከርና ውጤታማ ማድረግ አለባቸው ሲሉም አስገንዝበዋል። በተዘጋጀው የጋራ የትብብርና የቅንጅት ማዕቀፍ ሰነድ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የመምሪያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በታንዛንያ ተሸንፏል
Oct 22, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በ16ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ ከታንዛንያ አቻው ጋር ባደረገው የመጀመሪያ ጨዋታ የ2 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዷል። በአዛም ኮምፕሌክስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አይሻ ጁማ እና ጃሚላ ራጃብ ለታንዛንያ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሉሲዎቹ የመልስ ጨዋታቸውን ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ያደርጋሉ። የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ በመልሱ ጨዋታ ከሶስት እና ከዚያ በላይ ጎል በማስቆጠር ማሸነፍ ይጠበቅበታል።
በባሌ ዞን የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ስኬታማ ለማድረግ የውሃ መሳቢያ ፓምፕ ለአርሶ አደሮች እየተከፋፈለ ነው
Oct 22, 2025 51
ሮቤ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በባሌ ዞን የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ለማሳካት የውሃ መሳቢያ ሞተር ፓምፖችን ለአርሶ አደሩ እያከፋፈለ መሆኑን የዞኑ የመስኖና አርብቶ አደር ልማት ጽህፈት ቤት ገለጸ። ጽህፈት ቤቱ በ53 ማህበራት ስር ለተደራጁ የሲናና ወረዳ አርሶ አደሮች የውኃ መሳቢያ የሞተር ፓምፖችን ዛሬ አከፋፍሏል። የዞኑ የመስኖና አርብቶ አደር ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አወል ኡመር በወቅቱ እንደገለጹት አርሶ አደሩ በአካባቢው የሚገኙ የውኃ አማራጮችን በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ ነው። በ2018 ዓ.ም በበጋ ወራት በዞኑ በሚገኙ 10 ወረዳዎች 183 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ እንደሚለማ ተናግረዋል። እንዲሁም የዞኑ አርሶና አርብቶ አደሮች ከሰብል ልማት በተጓዳኝ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በመሰማራት በሚያገኙት ተጨማሪ ገቢ ውጤታማ እንዲሆኑ የሞተር ፓምፖቹ ትልቅ እገዛ እንደሚኖረቸው አክለዋል። እቅዱን ለማሳካት በማህበር ለተደራጁ የዞኑ አርሶ አደሮች 900 የውሃ መሳቢያ ሞተር ፓምፖችን የማከፋፋሉ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በሲናና ወረዳ በ53 ማህበር ለተደራጁ አርሶ አደሮች የተከፋፈሉ የውኃ መሳቢያ የሞተር ፓምፖች የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን አስረድተዋል። አቶ አወል እንዳሉት በዞኑ የዛሬውን ጨምሮ ባለፉት የለውጥ ዓመታት 7 ሺህ የሚሆኑ የውኃ መሳቢያ ሞተር ፓምፖች ለአርሶ አደሮች የተሰራጩ ሲሆን እነዚህም ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ማልማት እንደሚችሉ አስታውሰዋል። የተሰራጩት የውሃ መሳቢያ ፓምፖች አርሶ አደሩ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ጨምሮ በሌሎች ገበያ ተኮር የልማት ኢኒሼቲቮች ውጤታማ እንዲሆኑ እያገዙ መሆኑን ተናግረዋል። የሞተር ፓምፑን ከተረከቡ የሲናና ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል ሐሰን ከድር በሰጡት አስተያየት የሞተር ፓምፑ በተለምዶ የሚያከናውኑትን የመስኖ ልማት ሥራ ለማዘመን እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል። የውሃ መሳቢያ ሞተሩ ከዚህ በፊት ያጋጥማቸው የነበረውን የውኃ ብክነትን በመቀነስ በዘርፉ ውጤታማ ለመሆን እንደሚያስችላቸው የገለጹት ደግሞ የወረዳው አርሶ አደር ከተማ ፈይሳ ናቸው። አርሶ አደሮቹ የሞተር ፓምፑ በዓመት ሁለት ጊዜና ከዚያ በላይ በማልማት ውጤታማ ለመሆን እንደሚያግዛቸውም ተናግረዋል።
ፖለቲካ
ዘላቂ ሠላምን ለማረጋገጥ ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን - የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች
Oct 22, 2025 66
ጎንደር ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦በአካባቢያቸው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ተግባራት ውስጥ በመሳተፍ ያልተቆጠበ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጎንደር ከተማና የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች አስታወቁ። ሠላምና ልማት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ቄስ ሞገስ መልኬ እንዳሉት፤ የአካባቢው ሰላም ፀንቶ ልማት እንዲጠናከር በሚደረገው እንቅስቃሴ ወስጥ በንቃት በመሳተፍ ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል። በመንግስት የተናጠል ጥረት ብቻ ሠላምን ማረጋገጥ ስለማይቻል ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ የድርሻዬን ለማበርከት ዝግጁ ነኝ ያሉት ደግሞ አቶ መኮንን አዱኛ ናቸው። በአካባቢያቸው በሠላም ዘብ በመሳተፍ ሠላምን ለማስቀጠልና ህብረተሰቡ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያደርጉትን ድጋፍ እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። የሀገር ሽማግሌው አቶ ወልዴ መና በበኩላቸው፤ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ጎንደር በታሪኳ የማታውቀው የልማት ተቋዳሽ ለመሆን በቅታለች ነው ያሉት። በመሆኑም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች የበለጠ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሠላሟን ለማጠናከር በሚሰሩ ሥራዎች አበርክቷቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ሠላምና ልማት እንደማይነጣጠሉ በመገንዘብ ህዝቡ ሠላሙን ለማጽናት እያደረገ ላለው አስተዋጽኦ መንግስት እውቅና ይሰጣል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አላምረው አበራ ናቸው። በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ የተገኘው ሰላም ዘላቂ እንዲሆን ማህበረሰቡ የጀመረውን ድጋፍና እገዛ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው በበኩላቸው ህብረተሰቡ የሠላሙ ባለቤት በመሆኑ ጎንደር ከተማ የልማትና የሰላም ተጠቃሚ ሆናለች ብለዋል። የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ለከተማው ሠላም መረጋገጥ መስዋዕትነት ጭምር መክፈላቸውን ጠቁመው፤ ዛሬም ይህን ማህበራዊ ሃላፊነት አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። የጎንደርን ልማት፣ ሠላምና እድገት የማይሹ ሀይሎች በየጊዜው ለጥፋት እየተዘጋጁ በመሆኑ ህዝቡ ሠላሙን ሊያጠናክር ይገባል ብለዋል። በመድረኩ በከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አርሶ አደሮች ሴቶችና ወጣቶች ተሳታፊ ሆነዋል።
ሠራዊቱ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሰላምን የማፅናት ተግባሩን አጠናክሮ ቀጥሏል - ሜጀር ጄኔራል አድማሱ አለሙ
Oct 22, 2025 75
ወልዲያ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦መከላከያ ሠራዊት የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሰላምን የማፅናቱን ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን በመከላከያ ሠራዊት የ11ኛ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አድማሱ አለሙ ገለጹ። "ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሀሳብ በወልዲያ ከተማ የውይይት መድረክ ተካሄዷል። በውይይቱ ላይ የወልዲያ ከተማ አስተዳደር፣ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች እና የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል በመከላከያ የ11ኛ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል አድማሱ አለሙ እንዳመለከቱት፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጽንፈኛውን ቡድን ከአካባቢው የማፅዳት ተግባር በውጤማነት ቀጥሏል። ሠራዊቱ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሰላምን የማፅናት ሥራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸው፤ ለዚህ ስኬታማነት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አመልክተዋል። የሰሜን ምስራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው በበኩላቸው፤ ባዕዳን በራሳችን ወገኖች አጀንዳቸውን ለማስፈጸም የሚያደርጉት ሙከራ አይሳካም ሲሉ ገልጸዋል። የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዱባለ አብራሬ፤ ታሪካዊ ጠላቶቻችንና ተላላኪ ባንዳዎች በመቀናጀት የአካባቢውን ሠላም ለማደፍረስ እያደረጉት ያለውን ጥረት በጀግናው መከላከያና በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ እየመከነ ነው ብለዋል። ሰላምን አጽንቶ በማስቀጠል እድገትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ምሁራንና ሌላውም የሕብረተሰብ ክፍል ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል። የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አበበ ግርማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዩኒቨርሲቲው መምህራን የአካባቢውን ችግር ለመፍታት በእውቀትና በምርምር የታገዘ የመፍትሄ ሀሳብ ማፍለቅ ይጠበቅብናል ብለዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች ለአካባቢው ዘላቂ ሰላም የድርሻቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል።
የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈፀም አቅም በማጎልበት የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባራት ይጠናከራሉ-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Oct 22, 2025 106
ሆሳዕና፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈፀም አቅም በማሳደግ የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከክልሉ አመራር አካዳሚና ከብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር ለክልሉ አመራሮች ያዘጋጀው ስልጠና በሆሳዕና ከተማ እየተሰጠ ነው። "ብቁ አመራር ለላቀ ውጤት" በሚል መሪ ሀሳብ በሚሰጠው የአመራር ስልጠና ላይ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በየጊዜው የሚሰጡ ስልጠናዎች የአመራሩን አቅም በማሳደግ ሁለንተናዊ የልማት ውጤት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ስልጠናው የአመራሩን የመፈፀምና የማስፈጸም አቅም በማሳደግ የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እያገዙ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ስልጠናዎቹ ከነጠላ ትርክት ይልቅ አሰባሳቢና ገዥ ትርክትን በአመራሩ ላይ በማስረፅ የጋራ ሀገራዊ እሴቶችን ለማጠናከርም አቅም ስለሚፈጥሩ ይጠናከራሉ ብለዋል። በየደረጃው ያለው አመራርም ከስልጠናው የሚያገኘውን እውቀት በአግባቡ በመተግበር በክልሉ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ስኬታማ ለማድረግ ተግቶ እንዲሰራም አሳስበዋል። የክልሉ አመራር አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ብልሀቱ በበኩላቸው እንደገለጹት አካዳሚው ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚተጉ አመራሮችን እያፈራ ይገኛል፡፡ አካዳሚው ሀገራዊና ክልላዊ ተልዕኮዎችን በብቃት መፈፀም የሚችሉ አመራሮችን ለማፍራት የተለያዩ ስልጠናዎችን ከመስጠት ባለፈ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን እየሰራ መሆኑንም አክለዋል። ስልጠናው በክልሉ ለማከናወን የተያዙ የልማት እቅዶችን በመፈጸም የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማጠናከር አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል። ስልጠናውን እየሰጡ ያሉት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ሲሆኑ በስልጠናው የክልል፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡
የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ህብረብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል -የፌዴሬሽን ምክር ቤት
Oct 22, 2025 93
አዳማ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፡-የዘንድሮው 20ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ህብረብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር የፌዴሬሽን ምክር ቤት ገለጸ። 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በማስመልከት የትምህርት ተቋማት አመራሮችን በበዓሉ ላይ ግንዛቤ እንዲያስጨብጥ ያለመ የምክክር መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ በላይ ውድሻ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት ሀገርን ለመገንባትና ለማሳደግ ብዝሃነትን በአግባቡ መያዝና ማስተናገድ ይገባል። የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን እና ሌሎች አንድነትን የሚያጠናክሩ ሁነቶችን ማስተናገድ ደግሞ ብዝሃነትንና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በአግባቡ ለማስረጽ የጎላ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል። በዓሉን በየዓመቱ ማክበር ብቻ ሳይሆን ዜጎች በህገ መንግስት አስተምህሮ ዙሪያ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲይዙ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም አክለዋል። ባለፉት ዓመታት በፌዴራሊዝምና ህገ መንግስታዊ አስተምህሮ ላይ አተኩረው በተሰሩ ስራዎች በሀገር ልማትና ዕድገት ቀጣይነት፣ ህብረ ብሔራዊነትና የሀገር አንድነትን ከማፅናት አንፃር ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ለ20ኛ ጊዜ ዘንድሮ የሚከበረው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ህብረብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት የሚከናወኑበት መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም በፌዴሊዝምና ህገ መንግስት አስተምህሮ ዙሪያ ለዜጎች የተሻለ ግንዛቤ መፍጠር በሚያስችል መልኩ እንደሚከበርም ተናግረዋል። በዓሉን በታቀደው መሰረት ማክበር እንዲቻል ምሁራን፣ በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡም አስገንዝበዋል። የትምህርት ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የዘርፉ አመራሮችና ሙያተኞች በዓሉን ለማክበር በሚደረገው ሂደት ውስጥ ግንዛቤያቸው እንዲጎለብት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በትምህርት ተቋማት ያሉ ዜጎች ፌዴራሊዝምና የህገ መንግሥት አስተምህሮ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ጨብጠው ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር እንዲተጉ ያግዛል ብለዋል። 20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት እንደሚከበር መገለጹ ይታወሳል።
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሹመት አፀደቀ
Oct 22, 2025 99
ሐረር፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ):-የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት አስቸኳይ ጉባዔ የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሹመት አፀደቀ። በአስቸኳይ ጉባዔው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ አቶ ሳላህዲን ቶፊቅን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ ለምክር ቤቱ በእጩነት አቅርበዋል። በዚህም መሰረት ምክር ቤቱ በእጩነት የቀረቡትን አቶ ሳላህዲን ቶፊቅ፤ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው እንዲሰሩ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ። የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በመሆን የተሾሙት አቶ ሳላህዲን ቶፊቅ፤ በምክር ቤቱ አባላት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈፅመዋል። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት አስቸኳይ ጉባዔም ተጠናቋል።
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ማጠናከር ያለመ የሁለትዮሽ ምክክር አደረጉ
Oct 21, 2025 230
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር ዛሬ በሞስኮ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ ሚኒስትሮች የኢትዮጵያ እና ሩሲያን የረጅም ጊዜና ስትራቴጂካዊ አጋርነት የበለጠ ማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በጥልቀት መክረዋል። የሁለቱ ሀገራት የጋራ ትኩረቶች በሆኑ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይም ሀሳቦችን መለዋወጣቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በሩሲያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት ሞስኮ መግባታቸው ይታወቃል።
ሴቶች የአካባቢያቸውን ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ የሚያደርጉትን ተሳትፎ ማጠናከር አለባቸው
Oct 21, 2025 147
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፦በመዲናዋ ሴቶች ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት የአካባቢያቸውን ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ የሚያደርጉትን ተሳትፎ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ሀገር በቀል የሰላምና መቻቻል እሴቶች በትውልድ ግንባታ ላይ ያላቸው ፋይዳና ከሴቶች የሚጠበቀውን ሚና አስመልክቶ ከሴት አደረጃጀቶች ጋር ውይይት አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ ሊዲያ ግርማ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት ነው። በከተማው ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ህዝቡን የሰላም ባለቤት ለማድረግ በርካታ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሴቶች ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስጠበቅ የሚያደርጉትን ንቁ ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ሀይማኖታዊና የአደባባይ በዓላት እንዲሁም አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲካሄዱ ሴቶች ትልቅ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል። በመድረኩ የተገኙት ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ በሰላም ጉዳይ ግንባር ቀደም በመሆን ከጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት መወጣታችንን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Oct 21, 2025 188
ሆሳዕና ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ) :- በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቷ የሚስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ኮሚሽኑ ከዝግጅት ምዕራፍ በመጀመር በሁሉም አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አሁን ላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ እያካሄደ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ሂደት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ሁሉን አቀፍና አካታች የውይይት ሂደትን አጠናክሮ የቀጠለ መሆኑንም ማረጋገጥ ይቻላል። ከዚህ አንፃር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የምክክር ሂደቱ የሀገርን ችግር በባለቤትነት በመያዝ በምክክር መፍታት የምንችልበት ታሪካዊ አጋጣሚ ላይ እንገኛለን ብለዋል። የኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች በውይይት ለመፍታት በሚደረገው ታሪካዊ አጋጣሚ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ አረጋግጠዋል። በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የቁጥጥር መምሪያ ኃላፊና የሆሳዕና ደብረ መዊዕ ገዳም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቢ ትፍስኢት ቀሲስ ዳዊት አብርሃም፤ ለችግሮች ሁሉ መፍቻ መንገድ ከውይይት የበለጠ አዋጭና አትራፊ መንገድ የለም ይላሉ። በመሆኑም የሀገርን ችግሮች ተመካክሮ በመፍታት ለትውልዱ ሁሉ የተመቸችና ሰላም የሰፈነባት ሀገር ማጽናት የጋራ አደራና ሃላፊነታችን ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስትና ዜጎች ያለችግር የሚኖሩባት ሀገር ለመገንባት ያለ ልዩነት ለምክክር መሰባሰብ አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የአብሮነትንና የሰላም እሴቶችን ማጠናከር እንዲሁም ሰላምን ማስተማር የኃይማኖት አባቶች ዋነኛ ተልዕኮ መሆኑን አንስተው ለምክክሩ መሳካት የላቀ ሚናችንን ለመወጣት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የወጣቶች ተወካይ እስማኤል ሻሜቦ፤ በበኩሉ በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት እየሰራን እንገኛለን ይህንኑም አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ኮሚሽኑ የጀመራቸውን ስራዎች በማገዝ ረገድ በተለይም ቤተ እምነቶች ከፍተኛ ሃላፊነት ያለባቸው በመሆኑ በዚሁ ልክ ለማገዝ ተዘጋጅተናል ሲልም አረጋግጧል። የቡታጅራ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ላቀች ወሰኔ፤ በሀገር ጉዳይ ላይ ተቀራርበን በመወያየት ችግሮችን መፍታት ባለመቻላችን ብዙ ዋጋ ያስከፈለን በመሆኑ አሁን ላይ ሁላችንም ለምክክር ዝግጁ መሆን አለብን ብለዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ለሀገር ሰላም፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነትና ለልማት እቅዶች ስኬት በጋራ መትጋት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል። "እኛ ኢትዮጵያውያን በአብሮነት በመጓዝ ወደ ተሻለ ምዕራፍ እንድንደርስ የውስጥ ችግሮቻችንን በመነጋገርና በመወያየት የመፍታት ባህላችንን ማዳበር አለብን" ያሉት የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ምህረት ተስፋዬ ናቸው፡፡ የጠመንጃ ትግል ኪሳራ እንጂ ትርፍ የሌለው በመሆኑ የሰላምን አማራጭ ብቻ በመከተል በምክክር ለችግሮች መፍትሄ ይዘን መቅረብ ይጠበቅብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን "የሴቶች፣ የወጣቶችና የአካል ጉዳተኞች ሚናና አስተዋጽኦ ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር " በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ክልሎች የውይይት መድረኮች በመካሄድ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
ፖለቲካ
ዘላቂ ሠላምን ለማረጋገጥ ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን - የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች
Oct 22, 2025 66
ጎንደር ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦በአካባቢያቸው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ተግባራት ውስጥ በመሳተፍ ያልተቆጠበ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጎንደር ከተማና የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች አስታወቁ። ሠላምና ልማት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ቄስ ሞገስ መልኬ እንዳሉት፤ የአካባቢው ሰላም ፀንቶ ልማት እንዲጠናከር በሚደረገው እንቅስቃሴ ወስጥ በንቃት በመሳተፍ ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል። በመንግስት የተናጠል ጥረት ብቻ ሠላምን ማረጋገጥ ስለማይቻል ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ የድርሻዬን ለማበርከት ዝግጁ ነኝ ያሉት ደግሞ አቶ መኮንን አዱኛ ናቸው። በአካባቢያቸው በሠላም ዘብ በመሳተፍ ሠላምን ለማስቀጠልና ህብረተሰቡ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያደርጉትን ድጋፍ እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። የሀገር ሽማግሌው አቶ ወልዴ መና በበኩላቸው፤ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ጎንደር በታሪኳ የማታውቀው የልማት ተቋዳሽ ለመሆን በቅታለች ነው ያሉት። በመሆኑም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች የበለጠ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሠላሟን ለማጠናከር በሚሰሩ ሥራዎች አበርክቷቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ሠላምና ልማት እንደማይነጣጠሉ በመገንዘብ ህዝቡ ሠላሙን ለማጽናት እያደረገ ላለው አስተዋጽኦ መንግስት እውቅና ይሰጣል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አላምረው አበራ ናቸው። በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ የተገኘው ሰላም ዘላቂ እንዲሆን ማህበረሰቡ የጀመረውን ድጋፍና እገዛ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው በበኩላቸው ህብረተሰቡ የሠላሙ ባለቤት በመሆኑ ጎንደር ከተማ የልማትና የሰላም ተጠቃሚ ሆናለች ብለዋል። የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ለከተማው ሠላም መረጋገጥ መስዋዕትነት ጭምር መክፈላቸውን ጠቁመው፤ ዛሬም ይህን ማህበራዊ ሃላፊነት አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። የጎንደርን ልማት፣ ሠላምና እድገት የማይሹ ሀይሎች በየጊዜው ለጥፋት እየተዘጋጁ በመሆኑ ህዝቡ ሠላሙን ሊያጠናክር ይገባል ብለዋል። በመድረኩ በከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አርሶ አደሮች ሴቶችና ወጣቶች ተሳታፊ ሆነዋል።
ሠራዊቱ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሰላምን የማፅናት ተግባሩን አጠናክሮ ቀጥሏል - ሜጀር ጄኔራል አድማሱ አለሙ
Oct 22, 2025 75
ወልዲያ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦መከላከያ ሠራዊት የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሰላምን የማፅናቱን ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን በመከላከያ ሠራዊት የ11ኛ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አድማሱ አለሙ ገለጹ። "ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሀሳብ በወልዲያ ከተማ የውይይት መድረክ ተካሄዷል። በውይይቱ ላይ የወልዲያ ከተማ አስተዳደር፣ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች እና የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል በመከላከያ የ11ኛ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል አድማሱ አለሙ እንዳመለከቱት፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጽንፈኛውን ቡድን ከአካባቢው የማፅዳት ተግባር በውጤማነት ቀጥሏል። ሠራዊቱ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሰላምን የማፅናት ሥራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸው፤ ለዚህ ስኬታማነት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አመልክተዋል። የሰሜን ምስራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው በበኩላቸው፤ ባዕዳን በራሳችን ወገኖች አጀንዳቸውን ለማስፈጸም የሚያደርጉት ሙከራ አይሳካም ሲሉ ገልጸዋል። የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዱባለ አብራሬ፤ ታሪካዊ ጠላቶቻችንና ተላላኪ ባንዳዎች በመቀናጀት የአካባቢውን ሠላም ለማደፍረስ እያደረጉት ያለውን ጥረት በጀግናው መከላከያና በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ እየመከነ ነው ብለዋል። ሰላምን አጽንቶ በማስቀጠል እድገትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ምሁራንና ሌላውም የሕብረተሰብ ክፍል ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል። የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አበበ ግርማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዩኒቨርሲቲው መምህራን የአካባቢውን ችግር ለመፍታት በእውቀትና በምርምር የታገዘ የመፍትሄ ሀሳብ ማፍለቅ ይጠበቅብናል ብለዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች ለአካባቢው ዘላቂ ሰላም የድርሻቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል።
የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈፀም አቅም በማጎልበት የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባራት ይጠናከራሉ-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Oct 22, 2025 106
ሆሳዕና፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈፀም አቅም በማሳደግ የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከክልሉ አመራር አካዳሚና ከብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር ለክልሉ አመራሮች ያዘጋጀው ስልጠና በሆሳዕና ከተማ እየተሰጠ ነው። "ብቁ አመራር ለላቀ ውጤት" በሚል መሪ ሀሳብ በሚሰጠው የአመራር ስልጠና ላይ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በየጊዜው የሚሰጡ ስልጠናዎች የአመራሩን አቅም በማሳደግ ሁለንተናዊ የልማት ውጤት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ስልጠናው የአመራሩን የመፈፀምና የማስፈጸም አቅም በማሳደግ የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እያገዙ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ስልጠናዎቹ ከነጠላ ትርክት ይልቅ አሰባሳቢና ገዥ ትርክትን በአመራሩ ላይ በማስረፅ የጋራ ሀገራዊ እሴቶችን ለማጠናከርም አቅም ስለሚፈጥሩ ይጠናከራሉ ብለዋል። በየደረጃው ያለው አመራርም ከስልጠናው የሚያገኘውን እውቀት በአግባቡ በመተግበር በክልሉ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ስኬታማ ለማድረግ ተግቶ እንዲሰራም አሳስበዋል። የክልሉ አመራር አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ብልሀቱ በበኩላቸው እንደገለጹት አካዳሚው ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚተጉ አመራሮችን እያፈራ ይገኛል፡፡ አካዳሚው ሀገራዊና ክልላዊ ተልዕኮዎችን በብቃት መፈፀም የሚችሉ አመራሮችን ለማፍራት የተለያዩ ስልጠናዎችን ከመስጠት ባለፈ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን እየሰራ መሆኑንም አክለዋል። ስልጠናው በክልሉ ለማከናወን የተያዙ የልማት እቅዶችን በመፈጸም የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማጠናከር አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል። ስልጠናውን እየሰጡ ያሉት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ሲሆኑ በስልጠናው የክልል፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡
የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ህብረብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል -የፌዴሬሽን ምክር ቤት
Oct 22, 2025 93
አዳማ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፡-የዘንድሮው 20ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ህብረብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር የፌዴሬሽን ምክር ቤት ገለጸ። 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በማስመልከት የትምህርት ተቋማት አመራሮችን በበዓሉ ላይ ግንዛቤ እንዲያስጨብጥ ያለመ የምክክር መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ በላይ ውድሻ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት ሀገርን ለመገንባትና ለማሳደግ ብዝሃነትን በአግባቡ መያዝና ማስተናገድ ይገባል። የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን እና ሌሎች አንድነትን የሚያጠናክሩ ሁነቶችን ማስተናገድ ደግሞ ብዝሃነትንና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በአግባቡ ለማስረጽ የጎላ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል። በዓሉን በየዓመቱ ማክበር ብቻ ሳይሆን ዜጎች በህገ መንግስት አስተምህሮ ዙሪያ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲይዙ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም አክለዋል። ባለፉት ዓመታት በፌዴራሊዝምና ህገ መንግስታዊ አስተምህሮ ላይ አተኩረው በተሰሩ ስራዎች በሀገር ልማትና ዕድገት ቀጣይነት፣ ህብረ ብሔራዊነትና የሀገር አንድነትን ከማፅናት አንፃር ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ለ20ኛ ጊዜ ዘንድሮ የሚከበረው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ህብረብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት የሚከናወኑበት መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም በፌዴሊዝምና ህገ መንግስት አስተምህሮ ዙሪያ ለዜጎች የተሻለ ግንዛቤ መፍጠር በሚያስችል መልኩ እንደሚከበርም ተናግረዋል። በዓሉን በታቀደው መሰረት ማክበር እንዲቻል ምሁራን፣ በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡም አስገንዝበዋል። የትምህርት ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የዘርፉ አመራሮችና ሙያተኞች በዓሉን ለማክበር በሚደረገው ሂደት ውስጥ ግንዛቤያቸው እንዲጎለብት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በትምህርት ተቋማት ያሉ ዜጎች ፌዴራሊዝምና የህገ መንግሥት አስተምህሮ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ጨብጠው ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር እንዲተጉ ያግዛል ብለዋል። 20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት እንደሚከበር መገለጹ ይታወሳል።
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሹመት አፀደቀ
Oct 22, 2025 99
ሐረር፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ):-የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት አስቸኳይ ጉባዔ የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሹመት አፀደቀ። በአስቸኳይ ጉባዔው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ አቶ ሳላህዲን ቶፊቅን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ ለምክር ቤቱ በእጩነት አቅርበዋል። በዚህም መሰረት ምክር ቤቱ በእጩነት የቀረቡትን አቶ ሳላህዲን ቶፊቅ፤ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው እንዲሰሩ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ። የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በመሆን የተሾሙት አቶ ሳላህዲን ቶፊቅ፤ በምክር ቤቱ አባላት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈፅመዋል። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት አስቸኳይ ጉባዔም ተጠናቋል።
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ማጠናከር ያለመ የሁለትዮሽ ምክክር አደረጉ
Oct 21, 2025 230
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር ዛሬ በሞስኮ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ ሚኒስትሮች የኢትዮጵያ እና ሩሲያን የረጅም ጊዜና ስትራቴጂካዊ አጋርነት የበለጠ ማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በጥልቀት መክረዋል። የሁለቱ ሀገራት የጋራ ትኩረቶች በሆኑ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይም ሀሳቦችን መለዋወጣቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በሩሲያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት ሞስኮ መግባታቸው ይታወቃል።
ሴቶች የአካባቢያቸውን ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ የሚያደርጉትን ተሳትፎ ማጠናከር አለባቸው
Oct 21, 2025 147
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ)፦በመዲናዋ ሴቶች ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት የአካባቢያቸውን ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ የሚያደርጉትን ተሳትፎ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ሀገር በቀል የሰላምና መቻቻል እሴቶች በትውልድ ግንባታ ላይ ያላቸው ፋይዳና ከሴቶች የሚጠበቀውን ሚና አስመልክቶ ከሴት አደረጃጀቶች ጋር ውይይት አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ ሊዲያ ግርማ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት ነው። በከተማው ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ህዝቡን የሰላም ባለቤት ለማድረግ በርካታ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሴቶች ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስጠበቅ የሚያደርጉትን ንቁ ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ሀይማኖታዊና የአደባባይ በዓላት እንዲሁም አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲካሄዱ ሴቶች ትልቅ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል። በመድረኩ የተገኙት ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ በሰላም ጉዳይ ግንባር ቀደም በመሆን ከጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት መወጣታችንን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Oct 21, 2025 188
ሆሳዕና ፤ ጥቅምት 11/2018(ኢዜአ) :- በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቷ የሚስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ኮሚሽኑ ከዝግጅት ምዕራፍ በመጀመር በሁሉም አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አሁን ላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ እያካሄደ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ሂደት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ሁሉን አቀፍና አካታች የውይይት ሂደትን አጠናክሮ የቀጠለ መሆኑንም ማረጋገጥ ይቻላል። ከዚህ አንፃር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የምክክር ሂደቱ የሀገርን ችግር በባለቤትነት በመያዝ በምክክር መፍታት የምንችልበት ታሪካዊ አጋጣሚ ላይ እንገኛለን ብለዋል። የኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች በውይይት ለመፍታት በሚደረገው ታሪካዊ አጋጣሚ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ አረጋግጠዋል። በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የቁጥጥር መምሪያ ኃላፊና የሆሳዕና ደብረ መዊዕ ገዳም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቢ ትፍስኢት ቀሲስ ዳዊት አብርሃም፤ ለችግሮች ሁሉ መፍቻ መንገድ ከውይይት የበለጠ አዋጭና አትራፊ መንገድ የለም ይላሉ። በመሆኑም የሀገርን ችግሮች ተመካክሮ በመፍታት ለትውልዱ ሁሉ የተመቸችና ሰላም የሰፈነባት ሀገር ማጽናት የጋራ አደራና ሃላፊነታችን ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስትና ዜጎች ያለችግር የሚኖሩባት ሀገር ለመገንባት ያለ ልዩነት ለምክክር መሰባሰብ አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የአብሮነትንና የሰላም እሴቶችን ማጠናከር እንዲሁም ሰላምን ማስተማር የኃይማኖት አባቶች ዋነኛ ተልዕኮ መሆኑን አንስተው ለምክክሩ መሳካት የላቀ ሚናችንን ለመወጣት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የወጣቶች ተወካይ እስማኤል ሻሜቦ፤ በበኩሉ በምክክር ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት እየሰራን እንገኛለን ይህንኑም አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ኮሚሽኑ የጀመራቸውን ስራዎች በማገዝ ረገድ በተለይም ቤተ እምነቶች ከፍተኛ ሃላፊነት ያለባቸው በመሆኑ በዚሁ ልክ ለማገዝ ተዘጋጅተናል ሲልም አረጋግጧል። የቡታጅራ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ላቀች ወሰኔ፤ በሀገር ጉዳይ ላይ ተቀራርበን በመወያየት ችግሮችን መፍታት ባለመቻላችን ብዙ ዋጋ ያስከፈለን በመሆኑ አሁን ላይ ሁላችንም ለምክክር ዝግጁ መሆን አለብን ብለዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ ለሀገር ሰላም፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነትና ለልማት እቅዶች ስኬት በጋራ መትጋት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል። "እኛ ኢትዮጵያውያን በአብሮነት በመጓዝ ወደ ተሻለ ምዕራፍ እንድንደርስ የውስጥ ችግሮቻችንን በመነጋገርና በመወያየት የመፍታት ባህላችንን ማዳበር አለብን" ያሉት የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ምህረት ተስፋዬ ናቸው፡፡ የጠመንጃ ትግል ኪሳራ እንጂ ትርፍ የሌለው በመሆኑ የሰላምን አማራጭ ብቻ በመከተል በምክክር ለችግሮች መፍትሄ ይዘን መቅረብ ይጠበቅብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን "የሴቶች፣ የወጣቶችና የአካል ጉዳተኞች ሚናና አስተዋጽኦ ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር " በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ክልሎች የውይይት መድረኮች በመካሄድ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
ማህበራዊ
በአማራ ክልል የፍትህ አስተዳደር ሥርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 22, 2025 45
ባህር ዳር፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የፍትህ አስተዳደር ሥርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ። የፍትህ ቢሮውና የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በቅንጅት መስራት በሚያስችላቸው ተግባራት ላይ ያተኮረ የጋራ የትብብር ማዕቀፍ ሰነድ ዛሬ ተፈራርመዋል። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ብርሃኑ ጎሽም በመርሃ ግብሩ እንደገለጹት ወንጀሎችን ቀድሞ ለመከላከልና የፍትህ ስርዓቱን ለማዘመን በትኩረት እየተሰራ ነው። የፍትህ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ህብረተሰቡን በፍትሃዊነት ለማገልገል በቅንጅትና በትብበር መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል። ይህም በክልሉ ሰላም፣ ልማትና የህግ የበላይነትን በአስተማማኝ ሁኔታ በማረጋገጥ ጠንካራ የፍትህ ስርዓት በየደረጃው ለመገንባት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። የፍትህ ቢሮው እና የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ወንጀልን በመከላከል፣ ምርመራና ክስን በጥራትና በውጤታማነት በማከናወንና ሌሎች ስራዎችን በጋራ በመስራት ቅቡልነትን ማረጋገጥ ይገባል ነው ያሉት። ይህም የሃብት ብክነትን በመቀነስ፣ ጉልበትና ጊዜን በመቆጠብ ስኬትን በጋራ ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ገልጸው ዛሬ የተደረገው ስምምነትም ይህን የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት አገልግሎትን ለማጠናከር የፍትህና የፖሊስ ተቋማት በጋራ ተናበው መስራት አስፈላጊ ነው። የፖሊስና የፍትህ ተቋማት ተግባር የማይነጣጠሉ ናቸው ያሉት ኮሚሽነሩ ተቋማቱ ተቀናጅተውና ተናበው በመስራት የፍትህ አስተዳደር ስርዓቱን ማጠናከርና ውጤታማ ማድረግ አለባቸው ሲሉም አስገንዝበዋል። በተዘጋጀው የጋራ የትብብርና የቅንጅት ማዕቀፍ ሰነድ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የመምሪያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የፍትህ ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተዓማኒ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር ይገባል
Oct 22, 2025 52
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ የፍትህ ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተዓማኒ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። ቋሚ ኮሚቴው የፍትህ ሚኒስቴርን የ2018 እቅድ እና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ላይ ተወያይቷል። የቋሚ ኮሚቴው አባላት የፍትህ ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተዓማኒ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተከናወኑ ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ምን ይመስላሉ ሲሉ ጠይቀዋል። በማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ላይ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን ፈጥኖ ለማረም እየተከናወኑ ስላሉ ስራዎችም ጥያቄ አቅርበዋል። የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሀን (ዶ/ር) በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ የፍትህ ስርዓቱን ቀልጣፋና ተአማኒነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል። በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በህግ አወጣጥና ማሻሻያ ስራዎች እንዲሁም በመርታት ምጣኔ እና ፍርድን በማስፈጸም ውጤታማ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። አጠቃላይ ስርዓቱን ተአማኒ ማድረግ የሚያስችል ዲጂታል አሰራር መዘርጋቱንም ነው ያብራሩት። የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋዬ ዳባ በበኩላቸው እቅዱ በ2018 ለፍትህ እና ሰላም ዘርፍ የተሰጡ አቅጣጫዎችን ማእከል አድርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። ከባለድርሻ አካላት ጋር በተከናወኑ ቅንጅታዊ አሰራሮች የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን በመግለጽ። በማረሚያ ቤቶች የሚስተዋሉ ውስንነቶችን መፍታት የሚያስችል ሀገር አቀፍ ጥናት እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ ናቸው። በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ወደ ማረሚያ ቤት ከሚሄዱ ይልቅ ማህበረሰባዊ አገልግሎት የሚሰጡበትን ስርዓት የሚዘረጋ የአማራጭ ቅጣት ረቂቅ አዋጅ እየተዘጋጀ መሆኑን አንስተዋል። የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እጸገነት መንግስቱ የሚኒስቴሩ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ገልጸው ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በተቋማዊ አሰራርና አደረጃጀት ስራዎች ትምህርት የሚወሰድባቸው መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በቀጣይም በዲጂታላይዜሽን ላይ የጀመራቸውን ስራዎች ወደ ክልሎች ማስፋት እንደሚገባ አመላክተዋል።
የወጣት ማዕከላትን የስብዕና ማበልፀጊያ በማድረግ የወጣቶችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው
Oct 22, 2025 84
ባህር ዳር ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦የወጣት ማዕከላትን የስብዕና ማበልፀጊያ በማድረግ የወጣቶችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የሚኒስቴሩ የወጣቶች ዘርፍ አመራሮችና የአማራ ክልል የስራ ሃላፊዎች በባህር ዳር ከተማ የሚገኙ የወጣት ማእከላትንና የባህርዳር ብሄራዊ ስታዲየምን ዛሬ ጎብኝተዋል። በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የወጣቶች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አህመድ በወቅቱ እንደገለጹት በአገር አቀፍ ደረጃ ከ3ሺህ በላይ የወጣት ማዕከላት ይገኛሉ። እነዚህ የወጣት ማእከላት የወጣቱን ስብእና በመገንባት ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አብርክቶዋቸው በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን በጥናት መለየቱን ተናግረዋል። ይህን ችግርም በመቅረፍ ማእከላቱ በራሳቸው ገቢ በመተዳደር ለወጣቶች የመዝናኛና የማስተማሪያ አማራጭ በመሆን መልካም ዜጋ ለመገንባት እንዲያግዙ በአዲስ መልክ ለማደራጀት እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም የወጣቶች ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ከማዘውተሪያነት ወደ ወጣት ስብዕና ማበልጸጊያነት ለማምጣት የሦስት ወር ንቅናቄ መጀመሩን ጠቁመው የአምስት ዓመት የስብእና ግንባታ ስትራቴጅ እየተዘጋጀ ነው ብለዋል። ይህን ለማድረግም በባህር ዳር ከተማ የሚገኘው የሽምብጥ ሞዴል የወጣቶች ስብዕና ልማት ማዕከል በአሰራሩ፣ በአደረጃጀቱና ባለው ግብአት አርአያ በመሆኑ በተሞክሮነት ተወስዶ ወደ ሌሎች ለማስፋት እንደሚሰራ ገለጸዋል። የአማራ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ እርዚቅ ኢሳ በበኩላቸው በክልሉ ከሚገኙት 466 የወጣት ማእከላት ውስጥ 280 የሚሆኑት አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በባህርዳር ከተማ የሚገኘው የሽምብጥ ሞዴል የወጣቶች ስብዕና ልማት ማዕከልም ወጣቶችን ከማዝናናት ባለፈ የራሱን ገቢ በማመንጨት፣ በእርስ በእርስ መማማር፣ በስራ ፈጠራ ስልጠናና የምክር አገልግሎት በመስጠት አርአያ ነው ብለዋል። በቀጣይም የማእከሉን ተሞክሮ ወደ ሌሎች በማስፋት የወጣቱን ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በጅማ ከተማ ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት በመስጠት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች ናቸው - ሚኒስቴሩ
Oct 22, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ከተማ በመንግሥትና በግል ጤና ተቋማት ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ ገለፁ። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ፣ የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዎች፣ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችና አጋር ድርጅቶች በጅማ የሚካሄደውን 27ኛውን የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ አስመልክቶ በከተማው የሚገኙ የጤና ተቋማትን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም የጅማ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ማዕከል፣ የጅማ ከተማ ሞዴል ጤና ጣቢያ እና የኦዳ ሁሌ አጠቃላይ ሆስፒታልን የአገልግሎት አሰጣጥን ተመልክተዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት 27ኛው የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ "ዘላቂ ኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ለጠንካራ የጤና ሥርዓት" በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚካሄድ ተናግረዋል። በጉብኝቱ እንደሀገር በጤናው ዘርፍ በሽታን የመከላከያና አክሞ የማዳን ስትራቴጂ ማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን በተጨባጭ መመልከታቸውን ገልጸዋል። የጅማ ጤና ጣቢያ ለቀዳማይ ልጅነት፣ ለእናቶችና ህፃናት ጤና፣ ለተላላፊና ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች መከላከልና ለማኅበረሰብ ጤና አገልግሎት አሰጣጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል። የግሉ ዘርፍ በጤናው ዘርፍ ላይ ያለው አስተዋጽኦ የሜዲካል ቱሪዝምን ማስፋፋት የሚያስችል የተደራጀና ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ መመልከታቸውንም ነው የገለጹት። ይህም መንግሥት የግሉ ዘርፍ በስፋት እንዲሳተፍ ያቀረበውን ምቹ ሁኔታ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ እንንዳለ የተመለከትንበት ነው ብለዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ማዕከል በድንገተኛ ህክምና፣ በጨቅላ ህፃናት ህክምና፣ በካንሰር ህክምና እና የዐይን ባንክን በማቋቋም የጀመረው ሥራ ለሌሎች ምሳሌ እንደሚሆንም አንስተዋል። የኦክስጅን ማምረቻ በመክፈት ጭምር የጀመረው ተግባር የሚደነቅ መሆኑንና ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ባሻገር በህክምና አገልግሎት አበረታች ተግባራትን እያከናወነ እንዳለም ጠቅሰዋል።
ኢኮኖሚ
የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቀቂ አዋጅ ኢትዮጵያ ያላትን የዕጽዋት ሀብት ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመንከባከብ አቅም ይፈጥራል
Oct 22, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቀቂ አዋጅ መዘጋጀት ኢትዮጵያ ያላትን የዕጽዋት ሀብት ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለመንከባከብ አቅም እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ ገለጹ፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በዕጽዋት ጥበቃ እና ኳራንቲን ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት የአስረጂ መድረክ አካሂዷል። የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዕጽዋት ሀብት የታደለች የበርካታ ብዝሀ ህይወት መገኛ ብትሆንም የተፈጥሮ ሀብቷን በአግባቡ መጠቀም የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ የላትም፡፡ ከዚህ በፊት የነበረው ህግ የግብርናን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንቅፋት የሆነውን መጤና ወራሪ ተባይ ለመከላከል ውስንነት ነበረበት ብለዋል፡፡ በተለይም በዕጽዋት ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ ተባዮችን አስቀድሞ መከላከልና ጠንካራ የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት አያስችልም ነበር ነው ያሉት፡፡ በዚህም የዓለም አቀፍ የዕጽዋት ጥበቃ ስምምነትን መነሻ ያደረገ የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ የዕጽዋት ሀብቶቿ ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያገኙ እና መጤና ወራሪ ተባዮችን መከላከል የሚያስችል አቅም ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ይሄውም ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ ያላትን ተሳትፎ በማሳደግ ከዕጽዋት ዘርፍ የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንድታገኝ እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር)፤ መንግስት የግብርናን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቀቂ አዋጅ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ገልጸው፤ ተባይ በዕጽዋት ላይ የሚያደርሰውን የምርት ብክነት መቀነስና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ያስችላል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወንዳለ ሀብታሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ በዓለም አቀፍ ገበያ መወዳደር የሚያችሉ መስፈርቶችን የያዘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት በአግባቡ ጥቅም ለማዋል ወሳኝ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ የግብርና ኤክስቴንሽንን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል ነው
Oct 22, 2025 49
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ይፋዊ የባለድርሻ አካላት ውይይት አካሂዷል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የተዘጋጀው ከኢትዮጵያ የግብርና ዕድገት ጋር የሚራመድ የግብርና ኤክስቴንሽን ህግ በማስፈለጉ ነው፡፡ በረቂቅ አዋጁ ላይ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የረጅም ጊዜ ውይይትና ጥናት መደረጉን ገልጸው፤ በዚህም ከዘርፉ ተዋንያን ገንቢ አስተያየቶች ተሰጥተዋል፤ በግብዓትነትም ተካተዋል ብለዋል፡፡ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር) መንግስት የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን የሚፈለገውን ዕድገት ለማስመዝገብ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ በዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ እና አስተዳደር ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ያስችላል ብለዋል፡፡ በግብርና ኤክስቴንሽን ዘርፍ በመንግስት ብቻ ሲከናወኑ የነበሩ ተግባራት ላይ ሌሎችም የዘርፉ ተዋንያን እንዲሳተፉ የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፤ ዘርፉ ራሱን በቻለ ህግ እንዲመራ የሚያደርግ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ የግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወንዳለ ሀብታሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ የአርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ፍላጎት መነሻ በማድረግ ተሞክሮዎችን በሚያሰፋ መልኩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ልምድና እውቀት የያዘ መሆኑን ገልጸው፤ የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የጎላ አበርክቶ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
በባሌ ዞን የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ስኬታማ ለማድረግ የውሃ መሳቢያ ፓምፕ ለአርሶ አደሮች እየተከፋፈለ ነው
Oct 22, 2025 51
ሮቤ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በባሌ ዞን የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ለማሳካት የውሃ መሳቢያ ሞተር ፓምፖችን ለአርሶ አደሩ እያከፋፈለ መሆኑን የዞኑ የመስኖና አርብቶ አደር ልማት ጽህፈት ቤት ገለጸ። ጽህፈት ቤቱ በ53 ማህበራት ስር ለተደራጁ የሲናና ወረዳ አርሶ አደሮች የውኃ መሳቢያ የሞተር ፓምፖችን ዛሬ አከፋፍሏል። የዞኑ የመስኖና አርብቶ አደር ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አወል ኡመር በወቅቱ እንደገለጹት አርሶ አደሩ በአካባቢው የሚገኙ የውኃ አማራጮችን በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ ነው። በ2018 ዓ.ም በበጋ ወራት በዞኑ በሚገኙ 10 ወረዳዎች 183 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ እንደሚለማ ተናግረዋል። እንዲሁም የዞኑ አርሶና አርብቶ አደሮች ከሰብል ልማት በተጓዳኝ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በመሰማራት በሚያገኙት ተጨማሪ ገቢ ውጤታማ እንዲሆኑ የሞተር ፓምፖቹ ትልቅ እገዛ እንደሚኖረቸው አክለዋል። እቅዱን ለማሳካት በማህበር ለተደራጁ የዞኑ አርሶ አደሮች 900 የውሃ መሳቢያ ሞተር ፓምፖችን የማከፋፋሉ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በሲናና ወረዳ በ53 ማህበር ለተደራጁ አርሶ አደሮች የተከፋፈሉ የውኃ መሳቢያ የሞተር ፓምፖች የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን አስረድተዋል። አቶ አወል እንዳሉት በዞኑ የዛሬውን ጨምሮ ባለፉት የለውጥ ዓመታት 7 ሺህ የሚሆኑ የውኃ መሳቢያ ሞተር ፓምፖች ለአርሶ አደሮች የተሰራጩ ሲሆን እነዚህም ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ማልማት እንደሚችሉ አስታውሰዋል። የተሰራጩት የውሃ መሳቢያ ፓምፖች አርሶ አደሩ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ጨምሮ በሌሎች ገበያ ተኮር የልማት ኢኒሼቲቮች ውጤታማ እንዲሆኑ እያገዙ መሆኑን ተናግረዋል። የሞተር ፓምፑን ከተረከቡ የሲናና ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል ሐሰን ከድር በሰጡት አስተያየት የሞተር ፓምፑ በተለምዶ የሚያከናውኑትን የመስኖ ልማት ሥራ ለማዘመን እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል። የውሃ መሳቢያ ሞተሩ ከዚህ በፊት ያጋጥማቸው የነበረውን የውኃ ብክነትን በመቀነስ በዘርፉ ውጤታማ ለመሆን እንደሚያስችላቸው የገለጹት ደግሞ የወረዳው አርሶ አደር ከተማ ፈይሳ ናቸው። አርሶ አደሮቹ የሞተር ፓምፑ በዓመት ሁለት ጊዜና ከዚያ በላይ በማልማት ውጤታማ ለመሆን እንደሚያግዛቸውም ተናግረዋል።
አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ከእንስሳት ሃብት የበለጠ ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 22, 2025 141
ጂንካ ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሩን ከእንስሳት ሀብቱ የበለጠ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት እንደሚጠናከሩ የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ አስታወቀ። በደቡብ ኦሞ ዞን ጊዜያዊ የእርድ እንስሳት ማቆያ ማዕከላት ከ130 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሊገነቡ መሆኑም ተመልክቷል። ለዚህም በበናፀማይ ወረዳና በቱርሚ ከተማ አስተዳደር የተዘጋጀ የሳይት ርክክብ ተደርጓል። በቢሮ የአደጋ ስጋት ቅነሳና አካታች የኢኮኖሚ እሴት ማሻሻያ ፕሮጀክት አስተባባሪ ስዩም መታፈሪያ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ ደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሩን ከእንስሳት ሀብቱ የበለጠ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይጠናከራሉ። የአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ በሚያረባቸው እንስሳት ብዛት ልክ የበለጠ ተጠቃሚ ሳይሆን መቆየቱን አመልክተው በክልሉም ይህንን ከግምት ባስገባ መልኩ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። ለዚህም በዞኑ በናጸማይና ቱርሚ ከተማ የኤክስፖርት ስታንዳርድን ያሟሉ የእርድ እንስሳት ጊዜያዊ ማቆያ ማዕከላት ለመገንባት መታቀዱን ገልጸዋል። የኤክስፖርት ስታንዳርድ ያሟሉ የዕርድ እንስሳት ጊዜያዊ ማቆያ ማዕከላቱ መገንባት አርብቶ አደሩ ከእንስሳት ሀብት የሚገባውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንዲያገኝ ያስችላል ብለዋል። በክልሉ በአርብቶ አደር አካባቢ ያሉ እንስሳት ሀብትን ጥራት ጠብቆ በሀገሪቱ የሚገኙ ቄራዎችን ፍላጎት ያማከለ የዕርድ እንስሳት አቅርቦት እንዲኖር እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ አማካሪ መሀንዲስ ኢንጂነር አዳነ መንገሻ በበኩላቸው ፕሮጀክቶቹ እያንዳንዳቸው በሁለት ሄክታር መሬት ላይ እንደሚያርፉ ገልጸዋል። የፕሮጀክቶቹን ግንባታ በ6 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራና በዛሬው ዕለትም የግንባታ ቦታ ርክክብ መከናወኑን ነው የገለጹት። የሁለቱን ማዕከላት ግንባታ ለማከናወንም ከ130 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን ገልጸው በተያዘው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። የጊዜያዊ የዕርድ እንስሳት ማቆያ ማዕከላቱ የእንስሳት ክሊኒክ፣ መኖ ማከማቻ፣ የእንስሳት መመገቢያ እና ማረፊያ ክፍሎች ያሉት መሆኑንም ጠቁመዋል። በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ፣ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊዎች፣ የደቡብ ኦሞ ዞን ከፍተኛ አመራር አባላትና የአርብቶ አደሩ ተወካዮች ተገኝተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የአህጉሪቱን ወጣቶች የፈጠራ አቅም ማጎልበት ይገባል - ምክትል ሊቀ-መንበር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ
Oct 22, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ):- የበለፀገች አፍሪካን ለመገንባት ቴክኖሎጂና ፈጠራን ከአጀንዳ 2063 ጋር ማቀናጀትና የወጣቶችን የፈጠራ አቅም ማጎልበት እንደሚገባ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት የኢኖቬሽን ፌስቲቫል በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡ ፌስቲቫሉ "የአፍሪካ ህብረት ወጣቶችን የአህጉራዊ ኢኖቬሽን መሪ የማድረግ ተግባር" በሚል ርዕሰ ጉዳይ የሚካሄድ ሲሆን ኢኖቬተሮች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የግሉ ዘርፍ መሪዎች እና የወጣት ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ፌስቲቫሉ ለሀገር በቀል የኢኖቬሽን መፍትሄዎች እውቅና በመስጠት ስራዎችን የበለጠ ማላቅ ላይ ትኩረት የሚያደርግ መሆኑ ተመላክቷል። የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ ፈጠራንና ቴክኖሎጂን ከአጀንዳ 2063 ጋር በማቀናጀት የበለፀገች አፍሪካን ለመገንባት መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡ አፍሪካን ለመለወጥና ለማሳደግ ብሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን ፈጠራን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የአህጉሪቱ የፈጠራ ችሎታ፣ የዲጂታል ለውጥ እና የሥራ ፈጠራ ዋና አንቀሳቃሽ ኃይሎች ወጣቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ አህጉሪቱ በፈጠራ ዘርፍ የያዘችውን ግብ ማሳካት የሚችሉት ወጣቶች በመሆናቸው አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግላቸው ይገባል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የሴቶች፣ የጾታ እና ወጣቶች ዳይሬክተር ፕሩደንስ ንግዌንያ በበኩላቸው ወጣቶችና ሴቶች የአፍሪካን የፈጠራ ምህዳር መሠረት መጣል ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ አፍሪካ በፈጠራ ዘርፍ ማሳካት የምትፈልገውን ለውጥ እውን ለማድረግ በወጣቶችና ሴቶች የፈጠራ አቅም ላይ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ የፌስቲቫሉ ተሳታፊ ወጣት ትመር ብርሃኔ አፍሪካዊያን በቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ዘርፍ ያለንን ዕውቀት በየጊዜው ማላቅ አለብን ስትል ተናግራለች፡፡ ወጣት አሜን ቢኒያም በበኩሏ የምንፈልጋትን አፍሪካ እውን ለማድረግ ፈጠራን እና ቴክኖሎጂን ማሳደግ ተገቢ መሆኑን ጠቅሳ ለዘርፉ የሚደረገውን ድጋፍ በማጠናከር የተያዘው ግብ ስኬታማ ማድረግ የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝባለች፡፡ የኢኖቬሽን ፌስቲቫሉ እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአጀንዳ 2063 ግቦችን ለማሳካት፣ አካታችና ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ ራዕይ አቀጣጣይ እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝም ተገልጿል፡፡
የማር ጥራት ፍተሻን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ለማካሄድ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ ነው
Oct 22, 2025 94
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦የማር ምርትን የጥራት ፍተሻ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ለማካሄድ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አስታወቀ። ድርጅቱ ፍተሻውን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም ለማካሄድ ከተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነት መርሃ ግብር ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን ገልጿል። በኢትዮጵያ ከፍተኛ የማር ምርት አቅም ቢኖርም በሚፈለገው ልክ የውጭ ምንዛሬ እየተገኘበት አለመሆኑ የተገለጸ ሲሆን ለዚህ ደግሞ የማር ጥራት ጉዳይ አንዱና ዋነኛው ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የፍተሻ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ምትኩ ድሪባ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የማር ምርት ጥራትን ለማስጠበቅ የጸረ ተባይ ቅሪት ፍተሻ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም ለማካሄድ ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው። ለዚህም ከተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት ጋር በመተባበር እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ለፍተሻ የሚያስፈልጉ መሳሪያዎች ዝግጁ መደረጋቸውን አብራርተዋል። ፍተሻውን ለማከናወን ክህሎት ያለው ባለሙያ ያስፈልጋል ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ አሁን ላይ ከውጭ በመጣ አሰልጣኝ ለባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየተሰጠ ነው ብለዋል። ከዚህ ቀደም በማር ላይ የሚገኘውን የጸረ ተባይ ቅሪት ፍተሻ የሚደረገው ናሙና ወደ ውጭ ተልኮ መሆኑን አስታውሰው፤ አሁን ላይ ፍተሻውን ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እየሰራች መሆኑን ጠቁመው፤ ተወዳዳሪ ለመሆን መሰል የላብራቶሪ አቅም መገንባቱ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። የውጭ ምንዛሪ በማስቀረት ረገድም ፍተሻው በሀገር ውስጥ መካሄዱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል። በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምግብና መጠጥ ፍተሻ ላቦራቶሪ ሲኒየር አናሌቲካል ኬሚስት ብሩክ ስለሺ በበኩላቸው፤ የአቅም ግንባታ ስልጠናው በሌሎች ምርቶች ላይም የጸረ ተባይ ቅሪትን መፈተሽ የሚያስችል አቅም ለመገንባት ያስችላል ብለዋል። በተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነት መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሰለሞን መንገሻ በመርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የላቦራቶሪ አቅም እንዲገነባ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለላቦራቶሪ የሚያስፈልጉ የተለያዩ መሳሪያዎች ድጋፍ መደረጉን ገልጸው፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች የሥራ ላይ ስልጠና እንዲሰጡ እየተደረገ ነው ብለዋል። ለማር ምርት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች ተደራሽ መደረጋቸውን የገለጹት አስተባባሪው፤ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸው ሀገራት ልምድ ተቀምሮ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለዜጎች ፈጣን፣ ወጪ ቆጣቢና ፍትሃዊ አሰራርን ለመዘርጋት ያስችላል - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Oct 22, 2025 75
ጋምቤላ ፤ ጥቅምት 12/ 2018 (ኢዜአ) ፡- መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ወጪ ቆጣቢ አሰራርን በመዘርጋት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። በጋምቤላ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ተጀምሯል። በዚህ ወቅት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ እንደተናገሩት፤ በክልሉ የታቀደውን ልማትና እድገት በማፋጠን ለሕዝቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋና ዘመናዊ ማድረግ ያስፈልጋል። የተቋማትን አገልግሎት በአንድ ቦታ መስጠት የሚያስችለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ደግሞ እንግልትን በማስቀረት ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ወጪ ቆጣቢ አሰራርን በመዘርጋት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ማዕከሉ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው አንስተው፤ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ረገድም የጎላ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ለስኬታማነቱ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ (ዶ/ር)፤ እንደ ሀገር የታዩትን የልማት ስኬቶች ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሰው ተኮር የአገልግሎት ልህቀታችንን ልናጎለብት ይገባል ብለዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕድሴ ግድብ ግንባታ፣ የቱሪዝም መስህብ ማዕከላት ፣የከተሞች ኮሪደር ልማት፣ የሌማት ትሩፋትና ሌሎች የልማት ስኬቶች የኢትዮጵያ የማንሰራራት መገለጫ መሆናቸውን አንስተዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ መሰረታዊ ለውጥ ማስመዝገብ ፈተና ሆኖ መቆየቱን አስታውሰው፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተግባራዊ በማድረግ ሰው ተኮር የአገልግሎት ልህቀትን በመተግብር ለዜጎች ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት ተጀምሯል ብለዋል። በመሆኑም እንደ ሀገር የብልጽግና ጉዞን እውን ለማድረግ ለዜጎች የሚሰጠውን አገልግሎት ማዘመን ጊዜው የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። በክልሉ ለሕብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት የማዘመኑ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ላክዴር ላክባክ ናቸው። በክልል ደረጃ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በጋምቤላ ከተማ አስተዳደርና በዞን መዋቅሮችም የማስፋት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ኢኖቬሽንን የአፍሪካ ልማት ምሰሶ ለማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮች ገቢራዊ እየሆኑ ነው- የአፍሪካ ህብረት
Oct 22, 2025 93
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት ኢኖቬሽን ለአፍሪካ አካታች እና ዘላቂ ልማት አቀጣጣይ ሞተር ለማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት የኢኖቬሽን ፌስቲቫል በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል። “የአፍሪካ ህብረት ወጣቶችን የአህጉራዊ ኢኖቬሽን መሪ የማድረግ ተግባር” የፌስቲቫሉ መሪ ሀሳብ ነው። በፌስቲቫሉ ላይ ኢኖቬተሮች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የግሉ ዘርፍ መሪዎች እና የወጣቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ። ሁነቱ ለሀገር በቀል የኢኖቬሽን መፍትሄዎች እውቅና በመስጠት ስራዎችን የበለጠ ማላቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የአፍሪካ ብሩህ አዕምሮዎችን ከፋይናንስ አቅርቦት፣ ዘመኑ ከደረሰበት ክህሎት እና እድሎች ጋር በማገናኘት የኢኖቬሽን ስራዎችን የማሳደግ ፋይዳው የጎላ መሆኑም ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቷ ዜጎች የበለጸጉ የኢኖቬሽን መፍትሄዎች ድጋፍ በማድረግ እና ለወጣት መር የኢኖቬሽን ስራዎች ምቹ ምህዳር ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል። በህብረቱ የዲጂታል እና ኢኖቬሽን ፕሮግራም አማካኝነት ከ10 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ 18 ወጣት ኢኖቬተሮችን በተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች በማሰማራት ለኦፕሬሽን ፈተናዎች የተጠኑ የዲጂታል መፍትሄዎችን እንዲሰጡ እያደረገ መሆኑን ገልጿል። ፕሮግራሙን የሚደግፍ የአፍሪካ ህብረት የኦኖቬሽን ቤተ ሙከራ በማቋቋም ተቋማዊ የኢኖቬሽን አቅም ለመገንባት እና ትብብርን ለማጠናከር እየተጠቀመ እንደሚገኝም ነው ያስታወቀው። በዜጎች የቴክኖሎጂ ፈንድ አማካኝነትም 15 ኢኖቬተሮች ዜጎች በፖሊሲ ቀረጻ ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያሳድጉ መፍትሄዎችን እንዲያቀርቡ የፋይናንስ እና ቴክኒክ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። በተጨማሪም የአፍሪካ ህብረት እድሜያቸው ከ15 እስከ 25 የሆኑ ወጣት ሴት ኢኖቬተሮች በአህጉሪቷ ያሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በዲጂታል እና ቴክኖሎጂ አማራጮች እንዲፈቱ የቴክኒክ እና የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበት ኢኒሼቲቭ ገቢራዊ እያደረገ ነው። ይህም የስርዓተ ጾታ አካታችነት መሰረት ያደረገ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን እንዲድጉ የሚያስችል መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ህብረቱ ኢኖቬሽን የአጀንዳ 2063 ግቦችን ለማሳካት እና ሁሉን አካታችና ዘላቂ ልማት የማረጋገጥ ራዕይ አቀጣጣይ እንዲሆን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል። የኢኖቬሽን ፌስቲቫሉ እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በታንዛንያ ተሸንፏል
Oct 22, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በ16ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ ከታንዛንያ አቻው ጋር ባደረገው የመጀመሪያ ጨዋታ የ2 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዷል። በአዛም ኮምፕሌክስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አይሻ ጁማ እና ጃሚላ ራጃብ ለታንዛንያ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሉሲዎቹ የመልስ ጨዋታቸውን ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ያደርጋሉ። የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ በመልሱ ጨዋታ ከሶስት እና ከዚያ በላይ ጎል በማስቆጠር ማሸነፍ ይጠበቅበታል።
የአውሮፓ ኃያላኑ ሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱስ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Oct 22, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ):- በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ዘጠኝ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። በሳንቲያጎ በርናባው ስታዲየም ሪያል ማድሪድ ከጁቬንቱስ ምሽት 4 ሰዓት ላይ የሚያደርጉት ጨዋታ የተመልካቾችን ቀልብ ስቧል። የ15 ጊዜ የሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊ ሪያል ማድሪድ በሊግ ውድድር ፎርማቱ በስድስት ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። የሁለት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ጁቬንቱስ በሁለት ነጥብ 24 ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ክለቦች በሻምፒዮንስ ሊጉ ሲገናኙ ለ22ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 21 የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ 10 ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ ጁቬንቱስ ዘጠኝ ጊዜ ድል ቀንቶታል። ሁለት ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። በጨዋታዎቹ ሪያል ማድሪድ 25፣ ጁቬንቱስ 26 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ቡድኖቹ ለመጨረሻ ጊዜ በውድድሩ የተገናኙት እ.አ.አ በ2017/18 በሩብ ፍጻሜ ሲሆን ሪያል ማድሪድ በድምር ውጤት 4 ለ 3 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በ24 ነጥብ ሊጉን እየመራ የሚገኝ ሲሆን ጁቬንቱስ በሴሪአው በ12 ነጥብ 7ተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የቡድኖቹ የአውሮፓ መድረክ ፉክክር ከ60 ዓመት በላይ የዘለቀ ነው። የዛሬው ጨዋታም የዚሁ ተቀናቃኝነት ቀጣይ አካል ነው። የ45 ዓመቱ ስሎቬኒያዊ ስላቫኮ ቪንቺች የሁለቱ ቡድኖች ወሳኝ ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። ቼልሲ ከአያክስ፣ ኢንትራክት ፍራንክፈርት ከሊቨርፑል፣ ሞናኮ ከቶተንሃም ሆትስፐርስ፣ ባየር ሙኒክ ከክለብ ብሩዥ፣ ስፖርቲንግ ሊዝበን ከማርሴይ እና አትላንታ ከስላቪያ ፕራግ በተመሳሳይ ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አትሌቲኮ ቢልባኦ ከካራባግ እና ጋላታሳራይ ከቦዶ ግሊምት በተመሳሳይ ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ45 ላይ ይጫወታሉ።
ኢትዮጵያ በሴቶች እግር ኳስ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከታንዛንያ ጋር ዛሬ ጨዋታዋን ታደርጋለች
Oct 22, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሴቶች እግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን በ16ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከታንዛንያ አቻ ጋር ዛሬ ያከናውናል። የሁለቱ ሀገራት ጨዋታ ከቀኑ 11 ሰዓት በአዛም ኮምፕሌክስ ስታዲየም ይካሄዳል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ዩጋንዳን በደርሶ መልስ ውጤት በማሸነፍ ለመጨረሻው ዙር አልፋለች። ተጋጣሚዋ ታንዛንያ ኢኳቶሪያል ጊኒን በድምር ውጤት በማሸነፍ ወደ ወሳኙ ፍልሚያ ተሸጋግራለች። በአሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ የሚመራው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከታንዛንያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ ለአራት ሳምንታት ገደማ በአዲስ አበባ ዝግጅቱን አድርጓል። አሰልጣኝ ዮሴፍ ለጨዋታው ዝግጅት ሲያደርግ የነበረውን ስብስብ ወደ 21 በመቀነስ ወደ ታንዛንያ አምርቷል። ሮማን አምባዬ፣ ቤተልሄም መንተሎ፣ ፀጋ ንጉሤ፣ ቤዛዊት ንጉሤ እና ብዙዓየሁ ታደሰ (በጉዳት) ከስብስቡ የቀነሱ ተጫዋቾች መሆናቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። ሉሲዎቹ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ዳሬሰላም የገቡ ሲሆን ለጨዋታው የመጨረሻ ልምምዳቸውን በአዛም ኮምፕሌክስ ስታዲየም አድርገዋል። በባካሪ ሺሜ የሚመራው የታንዛንያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ለጨዋታው በዳሬ ሰላም ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ በውድድና የወዳጅነት ጨዋታዎች ላይ ሲገናኙ የአሁኑ ለስድስተኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው አምስት የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ሁለት ጊዜ ስታሸንፍ ታንዛንያ አንድ ጊዜ ድል ቀንቷታል። ሁለት ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። ኢትዮጵያ በጨዋታዎቹ ስድስት ግቦችን ስታስቆጥር ታንዛንያ ሰባት ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ሁለቱ ቡድኖች ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን እ.አ.አ በ2012 በጣምራ ባዘጋጁት 10ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ በመጨረሻው ዙር ማጣሪያ ተገናኝተው ኢትዮጵያ በድምር ውጤት በማሸነፍ ለውድድሩ ማለፏ አይዘነጋም። በፊፋ የሀገራት የእግር ኳስ ደረጃ ኢትዮጵያ 128ኛ፣ ታንዛንያ 131ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ዩጋንዳዊቷ አይሻ ናሉሊ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ትመራለች። የሁለቱ ሀገራት የማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኢትዮጵያ በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈች በታሪኳ ለአራተኛ ጊዜ በሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ መሳተፏን ታረጋግጣለች። በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ የሚደረጉ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ ጨዋታዎች ከጥቅምት 12 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ እንደሚካሄዱ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታውቋል። እ.አ.አ በ2026 በሞሮኮ አስተናጋጅነት በሚካሄደው 16ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇን ሀገር ጨምሮ 16 ሀገራት ይሳተፋሉ።
አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል
Oct 21, 2025 172
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 11/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተጠባቂ መርሃ ግብር አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን 4 ለ 0 ረቷል። ማምሻውን በኤምሬትስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቪክቶር ዮኮሬሽ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ጋብርኤል ማጋሌስ እና ጋብርኤል ማርቲኔሊ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። መድፈኞቹ ከእረፍት መልስ ያሳዩት ድንቅ የማጥቃት እንቅስቃሴ ጨዋታውን እንዲያሸንፉ አድርጓቸዋል። አርሰናል በሻምፒዮንስ ሊጉ ሶስተኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ ዘጠኝ ከፍ አድርጓል። አትሌቲኮ ማድሪድ በውድድሩ ሁለተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል። በሌሎች ጨዋታዎች የወቅቱ የዋንጫ ባለቤት ፒኤስጂ ባየር ሌቨርኩሰንን ከሜዳው ውጪ 7 ለ 2 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል። ዴዚሪ ዱዌ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኡስማን ዴምቤሌ፣ ክቪቻ ክቫራትሽኬሊያ፣ ቪቲኒያ፣ ዊሊያን ፓቾ እና ኑኖ ሜንዴዝ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። አሌክስ ጋርሺያ በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ለሌቨርኩሰን ግቦቹን አስቆጥሯል። ሮበርት አንድሪች ከሌቨርኩሰን፣ ኢልያ ዛባርኒ ከፒኤስጂ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል። ፒኤስጂ በዘጠኝ ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። ማንችስተር ሲቲ በአርሊንግ ሃላንድ እና በርናንዶ ሲልቫ ግቦች ቪያሪያልን 2 ለ 0 አሸንፏል። ኒውካስትል ዩናይትድ ቤኔፊካን 3 ለ 0 ረቷል። ሃርቪ ባርንስ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር አንቶኒ ጎርደን ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ፒኤስቪ ኤይንድሆቨን ናፖሊን 6 ለ 2፣ ኢንተር ሚላን ዩኒየን ሴይንት ዢሎሽን 4 ለ 0 እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ኮፐንሃገንን 4 ለ 2 አሸንፈዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በሚቀጥሉት አስር ቀናት በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ ዝናብ ያገኛሉ
Oct 22, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አስር ቀናት በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ቀደም ብሎ የክረምት ወቅት ዝናብ ሲያገኙ በነበሩት የምዕራብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ቀጣይነት ያለው ዝናብ ይኖራል። በሌላ በኩል በሰሜን ምዕራብ እና በሰሜን የሀገሪቱ ክፍሎች ወቅቱን ያልጠበቀ ቀላል መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች ያመላክታሉ ብሏል። የክረምት ወቅት ዝናብ እያገኙ የነበሩት የምዕራብና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚኖረው ርጥበት ለግብርና እንቅስቃሴ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ገልጿል። በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት አካባቢዎች የሚጠበቀው ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ርጥበት በወቅቱ ለሚጀመር የግብርና ስራ ከፍተኛ ጠቃሜታ ይኖረዋል ብሏል። አብዛኛው የበጋ ርጥበት ተጠቃሚ ተፋሰሶች እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን የተቀሩት ተፋሰሶች ዝቅተኛ ርጥበት እንደሚያገኙ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች ያሳያሉ። ባሮ አኮቦ፣ ኦሞ፣ ጊቤ፣ መካከለኛውና ታችኛው ስምጥ ሸለቆ፣ ላይኛውና መካከለኛው ገናሌ ዳዋ፣ ላይኛውና መካከለኛ ዋቢ ሸበሌ፣ ታችኛው ኦጋዴን፣ ታችኛው ዓባይ እና ታችኛው ተከዜ መካከለኛ ርጥበት እንደሚያገኙ በመግለጫው ተጠቅሷል።
በአማራ ክልል ከ260 ሺህ ሄክታር በሚልቅ መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ እቀባ ሥራ ይከናወናል
Oct 18, 2025 263
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዚህ ዓመት ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራዎች እንደሚከናወኑ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ንቅናቄ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ ልቼ ቀበሌ ተካሂዷል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) የተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ስራ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ካልመጣ የመስኖ ስራ ውጤታማ እንደማይሆን ገልጸዋል። ክልሉ በመስኖ መልማት የሚችል ሰፊ አቅም እንዳለው ተናግረዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግ በዚህ ዓመት ከ52 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዲስ መስኖ በማስገባት የክልሉን የመስኖ ልማት ወደ 383 ሺህ ሄክታር ከፍ ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቁመዋል። ከተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ስራዎች አንጻርም በዚህ ዓመት ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። ይህንንም ለማድረግ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን የሚሆን የደን እና የፍራፍሬ ችግኝ ልማት እቅድ ተይዞ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል። የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ዝግጅቶቹ የመስኖ አውታር ግንባታ፣ የቅየሳ፣ የአርሶ አደሮች ስልጠና እንዲሁም የችግኝ ጣቢያዎች ግንባታ እና የእርሻ መሳሪያ ዝግጅቶችን ያካተተ መሆኑን አንስተዋል። በተደረጉ ጥናቶች ክልሉ በመስኖ ሊለማ የሚችል 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት እንዳለው ገልጸዋል። ይህንን ለማልማትም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ ረገድ ባለፉት ዓመታት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በርካታ የውሃ መሳቢያ መሳሪያዎች ወደ ዞኖች እና ወረዳዎች መከፋፈሉን ገልጸው ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል ስራ መሆኑን ገልጸዋል።
ምርታማነትን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር ይገባል
Oct 18, 2025 178
አዳማ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፡-ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ የንቅናቄ ሳምንት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ዛሬ ተጀምሯል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ በወቅቱ እንዳመለከቱት፥ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራዎች የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር፣ድርቅና የጎርፍ አደጋዎችን ለመመከት አግዘዋል። በተለይም በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኖችን የመንከባከቡ ስራ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ለመቋቋምና የተራቆቱ መሬቶች እንዲያገግሙ፣የደረቁ ሃይቆች፣ወንዞችና ዥረቶች ተመልሰው ለመስኖና ለተለያዩ ልማቶች እንዲውሉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። በበጋ ወቅት የተገነቡ የተፋሰስ ልማቶችን በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ በመሸፈንና በመንከባከብ ውጤት መገኘቱንም አንስተዋል። ተግባሩንም ለማዝለቅ የችግኝ እንክብካቤ የንቅናቄ ሳምንትን በማወጅ በዛሬው ዕለት የክልሉ ግብርና ሴክተር አመራሮችና ሰራተኞች በምስራቅ ሸዋ ዞን ማስጀመራቸውን ጠቁመዋል። በችግኝ እንክብካቤው አረም በማንሳት፣የመኮትኮትና ውሃን በማጠጣት ችግኞቹ የበጋውን ወቅት እንዲቋቋሙ መስራት ይገባል ብለዋል። በንቅናቄው ማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት ከድር መሐመድ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ እንዲያድጉ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ችግኝ መትከል ብቻውን ግብ እንዳልሆነ ተናግረው፤የተተከሉትን ችግኞች በየጊዜው በመንከባከብ ለውጤት እንዲበቁ ማድረግ አለብን ብለዋል። ዘርፌ ማሞ በበኩሏ፥ በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ በቀዳሚነት የሚጎዱት ሴቶች በመሆናቸው ለመፍትሔው ላለፉት ሰባት ዓመታት በችግኝ ተከላና እንክብካቤ ላይ መሳተፋቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ ናት- ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)
Oct 16, 2025 262
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርኃ ግብር አካሂዷል። በመርኃ ግብሩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያሥላሴ፣ ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተገኝተዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ምላሽ ለመስጠት ያለንን ቁርጠኝነት ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። ጉባዔው አፍሪካውያን ለአየር ንብረት ለውጥ ተጨባጭ መፍትሔዎችን በመውሰድ ግንባር ቀደም መሆናቸውን ለዓለም በማሳየት ስኬታማ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም ለጋራ ችግሮች በጋራ ምላሽ ለመስጠት አቅማቸውን ያጠናከሩበት እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ይህን ስኬት ተጠቅሞ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በቀጣናው መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከል የተጀመሩ የቅንጅት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኢጋድ
Oct 20, 2025 168
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኢጋድ ሶስተኛው የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ በኬንያ ናይሮቢ ተጀምሯል። “በኢጋድ ቀጣና ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሰራተኛ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር ህጋዊ ማዕቀፍን ማሻሻል” የስብሰባው መሪ ቃል ነው። በስብሰባው ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት የሰራተኛ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች፣ ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(አይኤልኦ)፣ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(አይኦኤም)፣ የአውሮፓ ህብረትና የልማት አጋሮች ተገኝተዋል። በኢጋድ ቀጣና የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በቀይ ባህር መስመር ያለውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ከኢጋድ ቀጣና ውጪ የሚገኙ ዜጎች አባል ሀገራትን በነጠላ የመግቢያ ቪዛ መጎብኘት የሚያስችላቸውን የቪዛ ኢኒሼቲቭ ይፋ ይደረጋል። ኢኒሼቲቩ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርና ድንበር ተሻጋሪ ንግድን ማሳለጥ እንዲሁም ቱሪዝምን የማሳደግ ፋይዳ እንዳለው ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአውሮፓ ህብረት የፋይናንስ ድጋፍ የሚተገበረው ነጻ የሰዎችና የቁም እንስሳት እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፍ ሁለተኛ ምዕራፍ ይፋ ይሆናል። ማዕቀፉ ህጋዊ የፍልሰት መንገዶች ለማጠናከር እና ቀጣናዊ ትስስርን የማሳካት ግብ ያለው መሆኑንም አመልክቷል። ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሰንሰለትን መበጣጠስ፣ በፍልሰት በሌላ ሀገር የሚገኙ ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ላይ ምክክር ያደርጋሉ። በውይይቱ ማብቂያ ሀገራት የጋራ መግለጫ እንደሚያወጡ የሚጠበቅ ሲሆን ደህንነቱ የተጠበቀ መደበኛ ፍልሰት፣ ጠንካራ የሰራተኛ አስተዳደር ስርዓት መፍጠርና ለሰዎች ዝውውር የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ መስጠት ላይ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እንደሚገልጹ ተጠቁሟል። ኢጋድ በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የጋራ ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክቷል። ዜጎች ህጋዊ አማራጮችን እንዲከተሉና የኢኮኖሚ ፈተናን ጨምሮ ለሌሎች ገፊ ምክንያቶች ዘላቂ መፍትሄ መስጠት በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ ገልጿል። ስብሰባው ጥቅምት 10 እና 11 በባለሙያዎች፣ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚኒስትሮች ደረጃ ይካሄዳል።
የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በቁርጠኝነት ሊተገብሩ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት
Oct 19, 2025 209
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) አፈጻጸም ውጤታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብስባ ከጥቅምት 11 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገም እና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስ እና ዘላቂ የውሃና ተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚከናውን ኢዜአ ከህብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ
Oct 15, 2025 364
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር እና በአህጉሪቷ የማካካሻ ፍትህን ለማረጋገጥ በበለጠ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን በአፍሪካ ደረጃ ዛሬ በአህጉሪቷ መዲና አዲስ አበባ ዛሬ ይከበራል። “የገጠር ሴቶችን በማካካሻ ፍትህ አማካኝነት ማብቃት፤ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ስርዓተ ምግብን ማረጋገጥ” የቀኑ መሪ ሀሳብ ነው። በቀኑ አከባበር ላይ የአፍሪካ ህብረት አመራሮች፣ የመንግስታት ተወካዮች፣ የገጠር ሴቶች አመራሮች እና ተወካዮች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ የዳያስፖራ ተወካዮች፣ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ይሳተፋሉ። የቀኑ አከባበር አካል የሆነ የቴክኒክ ውይይት ትናንት የተካሄደ ሲሆን የአፍሪካ የገጠር ሴቶች መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ባለሙያዎች ሴቶችን ለማብቃት በየሀገራቱ እየተተገበሩ ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ የእውቀት እና የተሞክሮ ልውውጥ አድርገዋል። ዛሬ በሚኖረው ዋናው የቀኑ አከባበር የከፍተኛ ባለስልጣናት ቁልፍ ንግግሮች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የገጠር ሴቶች ኢኒሼቲቭ የተሞክሮ ማጋራት መርሃ ግብሮች እና አውደ ርዕዮች ይካሄዳሉ። ሁነቶቹ የገጠር ሴቶች በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እና በግብርና መካናይዜሽን አማካኝነት የሚበቁባቸው የኢኖቬሽን አማራጮች የሚቀርቡባቸው ናቸው። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን ከአፍሪካ ህብረት የ2025 መሪ ሀሳብ ከሆነው “የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” የተሳሳረ መሆኑ ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የማሻሻሻ ፍትህ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አካሄድ መሆኑን አመልክቷል። የቀኑን አከባበር ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የጋራ መግለጫው አፍሪካ ስርዓተ ጾታን ባማከለ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ስራ፣ የገጠር ሴቶችን በማብቃት እንዲሁም ማካካሻ ፍትህ እኩልነት የተረጋገጠበትና የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመገንባት ያላትን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት እንደሆነ ተገልጿል። የዓለም የገጠር ሴቶች ቀን የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማረጋገጥ እና በማካካኛ ፍትህ አማካኝነት በገጠሪቷ የአፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። ህብረቱ ቀኑን ሲያከብር የበለጸገች፣ ሁሉን አቃፊ እና ዘላቂነትን ያረጋገጠች አህጉር ለመገንባት ባለው መሻት ውስጥ ሴቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ወደኋላ እንዳይቀሩ ዳግም ቃል ኪዳኑን የሚያድስበት እንደሆነ አመልክቷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እ.አ.አ በ2007 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ባፀደቀው የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 62/136 አማካኝነት ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን እ.አ.አ ኦክቶበር 15 እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ በገጠር የሚገኙ ሴቶች ለግብርና፣ ምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ዘላቂ ልማት ያላቸው ወሳኝ አበርክቶዎች የሚዘከርበት ነው።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በሙሉ አቅም መተግበር ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው - መሐመድ አሊ ዩሱፍ
Oct 10, 2025 493
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ሙሉ ለሙሉ ገቢራዊ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁነቶች በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት እና ተወዳዳሪነት ተጽእኖ እያሳደሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከመቼው ጊዜ በላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ ለሙሉ በአፋጣኝ መተግበር እንደሚገባው የሚያመላክት ነው ብለዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ከቀረጥ ጋር ያልተያያዙ የንግድ ገደቦችን በማንሳት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተሳለጠ የንግድ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችሉ ማዕቀፎችን በመተግበር ለአጀንዳ 2063 መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኮሜሳ፣ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳዴቅ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) የሶስትዮሽ ትብብር ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕቀፉ የትስስር አጀንዳ ተምሳሌት እና አንድ የሆነች፣ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች አህጉር ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ቀጣናዊና አህጉራዊ የትስስር አጀንዳዎችን ትግበራ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 412
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 499
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 700
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
"ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 786
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ። አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው። ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል። ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡ ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1164
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1822
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2637
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2777
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 472
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 399
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6248
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4726
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የአፍሪካ የግብርና፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ፤ እድሎች እና ፈተናዎች
Oct 20, 2025 218
አፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማሳካትና እንድትበለጽግ የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ መዕራፍ ላይ ይገኛል። የአህጉሪቱን የመለወጥ ትልም ባሏት እምቅ ተፈጥሯዊ ጸጋዎች ላይ የተመረኮዘ ነው። ተዝቆ የማያልቀው የአፍሪካ ብዝሃ ሀብት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግና አይበገሬ አቅም መገባንት የሚያስችሏትም ጭምር ናቸው። ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ ሀብቶቿ እና ብዝሃ ከባቢ የአየር ንብረቷ ከሀብቶቿ መካከል ይጠቀሳሉ። ግብርና አሁንም የአፍሪካ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው። ዘርፉ ለአህጉሪቱ 35 በመቶ የሚጠጋ አጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት(ጂዲፒ) አስተዋጽኦ ያደርጋል። 60 በመቶ ህዝብም በግብርና ስራ እንደሚተዳደር የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) ሰነድ ያሳያል። ከዚህም ውስጥ አብዛኞቹ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። ሴቶች በግብርናው ዘርፍ ካለው የሰው ኃይል የ50 በመቶ ድርሻው ይወስዳሉ። የአፍሪካ ህዝብ 60 በመቶ ድርሻ የያዘው ወጣት በግብርና ንግድ፣ እሴት መጨመርና የኢኖቬሽን ስራዎች ያለው ተሳትፎ እያደገ መጥቷል። የዓለም 60 በመቶ ያልለማ መሬት ያለው በአፍሪካ ነው። ሰፊ የውሃ ሀብቶችና እያደገ ያመጣው ብሉ ኢኮኖሚ(የባህር እና ሌሎች የውሃ ሀብቶች) ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ እድገትን የሚያረጋግጡ ናቸው። የመሰረተ ልማቶች ተደራሽነት ማደግ፣ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችና ኢኖቬሽንን የተመረኮዙ የፋይናንስ አማራጮችን መስፋት ግብርናን የምግብ ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለኢንዱስትሪ ልማት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ እና ንግድ መሳለጥ ትልቅ አቅም መሆን ይችላል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በግብርና ምርቶችና አገልግሎቶች ያለውን አህጉራዊ የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ በማሳደግ ረገድ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ ነው። የንግድ ቀጣናውን በሚገባ መጠቀም ከተቻለ እ.አ.አ በ2030 የግብርና ንግድ ልውውጡን በ30 በመቶ ማሳደግ እንደሚቻል ጥናቶች ያመለክታሉ። ግብርናው የተጠቀሱት ጥንካሬዎች ያሉት ቢሆንም ረጅም ጊዜ የዘለቁ መዋቅራዊ ፈተናዎች አብረውት ዘልቀዋል። የግብርና ምርቶች ላይ የሚፈለገውን ያህል እሴት አለመጨመር፣ የቴክኖሎጂ አጠቀቃምና የምርታማነት ውስንነት፣ የመሰረተ ልማቶች እና ሎጅስቲክስ በበቂ ሁኔታ አለመሟላት፣ ተቋማዊና አስተዳደራዊ ክፍተቶች ከአየር ንብረት ለውጥና ሌሎች ተፈጥሯዊ አደጋዎች እንዲሁም እያደገ ከመጣው ህዝብ ጋር ተዳምሮ ግብርናውን እየፈተነው ይገኛል። ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ማጠንጠኛ የሆነው ጉዳይ የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት(ካዳፕ) ነው። እ.አ.አ በ2003 የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ ባደረገው ስብሰባ የግብርና የምግብ ዋስትና ድንጋጌን አጽድቋል። ይህ ማዕቀፍ የማፑቶ ድንጋጌ ስያሜን በማግኘት የካዳፕ ትግበራ በይፋ እንዲጀመር አድርጓል። የማፑቶ ድንጋጌ እ.አ.አ በ2014 በማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025 የተተገበረ) በአዲስ መልክ የታደሰ ሲሆን የተለያዩ ቃል ኪዳኖችን በውስጡ ይዟል። ይህም በካዳፕ አማካኝነት የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ከአጠቃላይ ዓመታዊ ጥቅል ምርታቸው(ጂዲፒ) ቢያንስ ስድስት በመቶውን ለግብርናው ዘርፍ እንደሚመድቡና በየሀገራቱ በዘርፉ በየዓመቱ በአማካይ ስድስት በመቶ እድገትን የማሳካት ግብ አለው። ረሃብን ማጥፋት፣ ድህነትን በግማሽ መቀነስ፣ የማይበገር አቅም መገንባትና የጋራ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ሌሎች ግቦች ናቸው። ካዳፕ የአፍሪካ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ያላቸውን ኢንቨስተመንት በማሳደግ፣ በአፍሪካ የእርስ በእርስ የግብርና ንግድን በማሳደግና የፖሊሲ መሰናሰልን በመፍጠር ቁልፍ ሚና ተወጥቷል። ይሁንና የተመዘገቡት ውጤቶች ያልተመጣጠነ ልዩነት የሚታይባቸው ናቸው። የ2023 የካዳፕ የግምገማ ሪፖርት እንደሚያሳየው የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የማላቦ ግቦችን ማሳደግ የሚያስችል መንገድ ላይ እንዳልሆኑ ያስቀምጣል። ይሁንና 26 ሀገራት በተቀመጡ ግቦች መመዘኛ መሻሻል እንዳሳዩ ይገልጻል። ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ካሜሮን፣ ግብጽ፣ ማሊ፣ ጋና እና ጋምቢያ የተሻለ አፈጻጸም ካላቸው ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ። አብዛኞቹ ሀገራት በግብርና ኢንቨስትመንት፣ ምርታማነት እና የፖሊሲ ትግበራ ላይ ፈተናዎች እንዳሉበት ሪፖርቱ አመልክቷል። ሀገራት የሰነዱን ትግበራ ማፋጠንና ተቋማዊ ቅንጅትን ማጠናከር እንደሚገባቸው አሳስቧል። የማላቦ ድንጋጌ ወደ መገባደዱ ላይ የሚገኝ ሲሆን የካዳፕ ቀጣዩ ምዕራፍ የካምፓላ ድንጋጌ ነው። ይህ የትግበራ ምዕራፍ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚቆይ ነው። የካምፓላ ድንጋጌ ከማፑቶ እና ማላቦ ድንጋጌዎች ትምህርቶችን በመውሰድ የግብናውን እድገት ማላቅ ግቡ አድርጎ ይዟል። የካምፓላ አጀንዳ ኢኖቬሽን፣ ዲጂታላይዜሽን፣ አረንጓዴ እድገት እና አይበገሬነት ያላቸውን ሚና በማንሳት መስኮቹ ስርዓተ ምግብን ዘላቂና አካታች የማድረግ ግብን ማሳካት እንደሚያስችሉ አመልክቷል። በዚህ ማዕቀፍ እ.አ.አ 2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ህዝብ ይኖራታል ተብሎ የሚጠበቀውን አፍሪካን በራስ አቅም የመመገብ ውጥን የያዘ ነው። ይሁንና የግብርና ምርታማነት ከዓለም አቀፍ አማካይ የምርታማነት ምጣኔ አንጻር ሲታይ አሁንም ወደ ኋላ ቀረት ያለ ነው። ይህም አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች የተገደበ የፋይናንስ አቅርቦት ማግኘታቸው እንዲሁም የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትና የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው አለመደረጉ የችግሩ አብይ መንስኤ ሆኖ ይጠቀሳል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎችና የከባቢ አየር ብክለት ፈተናዎቹ እንዲበረቱ አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ የበይነ መንግስታት ፓናል(IPCC) አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እርምጃዎችን በፍጥነት ካልወሰደች እ.አ.አ በ2050 የግብርና ምርታማነቷ ከ20 እስከ 30 በመቶ ሊቀንስ እንደሚችል ገምቷል። ከ250 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ አፍሪካውያን ደህንነቱ ያልተረጋገጠ እና ንጽህናው ያልተጠበቀ የውሃ አቅርቦት ፈተና ውስጥ ይገኛሉ። በህዝብ ቁጥር መጨመር፣ በከተሜነትና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ምክንያት ንጹህ የውሃ አቅርቦትን የማግኘት ጉዳይ የበለጠ ሊስፋ እንደሚችል ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩና ፈተናዎች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ለአባል ሀገራት የፋይናንስ እና የቴክኒክ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል። የህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር የስራ ክፍሉ(DARBE) አማካኝነት የአፍሪካን ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞችና ኢኒሼቲቮች የተናበቡና የጋራ ግብ ያላቸው እንዲሆኑ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል። የአቅም ግንባታ፣ የቴክኒክ እና የፖሊሲ ድጋፍም የሚያደርግ ሲሆን ብሄራዊ እቅዶች ከአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሰነዶችና የአጋርነት ማዕቀፎች ጋር የተጣጠሙ መሆናቸውን ያረጋገጣል። የስራ ክፍሉ ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች ጋር አጋርነቶችን የማጠናከር ስራ ያከናውናል። ግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት እንዲሁም የተፈጥሮ እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በዘላቂነት መጠቀም ላይ የተቀናጁ አሰራሮችን መፍጠር ላይም ይሰራል። የዘርፉ አጠቃላይ ስራዎች አካል የሆነው ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎችና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገምና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም(ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ(ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስና ዘላቂ የውሃና የተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩም ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚያከናውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። አፍሪካ ወደ ዘላቂ ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር እና አካባቢ ጥበቃ እያደረገች ያለው ጉዞ አንገብጋቢ አጀንዳና ሽግግሩን ለማፋጠን ወሳኝ ሚና አለው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የፋይናንስ ማነቆ፣ መሰረተ ልማቶች እና የፖሊሲ የመፈጸም አቅም ውስንነትን ጨምሮ የተለያዩ ፈተናዎች ቢኖሩባትም እድሎቿ ፈርጀ ብዙ ናቸው። በርካታ ያልለማ መሬት፣ ሰፊ የውሃ ሀብት፣ ወጣቶች እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በአፍሪካ ዘላቂ የግብርና እድገት ለማረጋገጥና ሁሉን አቀፍ ስርዓተ ምግብ ለመገንባት የሚያስችል ነው። ለአርሶ አደሮች በቂ የፋይናንስ አቅርቦት ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ አቅማቸውን መገንባት ቁልፍ ጉዳይ ነው። ሀገራት ብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸውን ከአህጉራዊ ማዕቀፎች ጋር ማጣጣም ይኖርባቸዋል። ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ይገባል። የተፈጥሮ ሀብትን በሚገባ መጠቀም፣ በኢኖቬሽን ላይ መዋዕለ ንዋይን ፈሰስ ማድረግና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች፣ አረንጓዴ እና የበለጸገች አህጉር መገንባት ይቻላል።
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 906
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡ በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!