ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በጋምቤላ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሂደት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል
Jun 6, 2026 93
ጋምቤላ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከአጋር አካላት ጋር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። በጋምቤላ ክልል ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በማስቀረት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን የሚገመግም መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሄዷል።   የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አርያት ኡጁሉ በመድረኩ እንደገለጹት፤ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በማስቀረት የሴቶችን የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ያስፈልጋል። በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ያለእድሜ ጋብቻ፣ በጋብቻ ላይ ጋብቻና ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በሴቶች ላይ የሚያደርሱት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት ከጎጂ ልማድ ጋር ተያይዞ ሴቶች ላይ ይደርስ የነበረውን ችግር በማስቀረት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ለውጦች መምጣታቸውን ተናግረዋል። በተለይም ቢሮው ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት ሴቶችን በእርሻ ልማት፣ በእርባታና ሌሎች የገቢ ማስገኛ ስራዎች በማሰማራት በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ረገድ አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል። የተገኙትን ለውጦች ይበልጥ ለማጠናከር አሁንም የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በቢሮው ግንዛቤ ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ግሩም ገብረኢየሱስ እንዳሉት፤ በክልሉ በሁሉም ቀበሌዎች የጎጂ ልማዳዊ ድርጊት አስወጋጅ ኮሚቴ በማቋቋም ያለእድሜ ጋብቻን ጨምሮ ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቀረት በትኩረት እየተሰራ ነው። ቢሮው ከጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቀረት የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። መድረኩ ላይ የክልሉ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን፣ በተከናወኑት ስራዎች ዙሪያ ሪፖርቶች ቀርበው ተገምግመዋል። በውይይት መድረኩ መጨረሻ አቅም ለሌላቸው ሴቶች የእርባታ ፍየሎችና የገንዘብ ድጋፍ ለተወካዮቻቸው ተበርክቷል።
በሮም እና ሞስኮ የደመቁት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች
Jun 6, 2026 76
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሮምና በሞስኮ በተካሄዱ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ድል አስመዝግበዋል። የዘንድሮው የዝናሜንስኪ ሜሞሪያል አትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ደማቅ ድል የተመዘገበበት መድረክ ሆኗል። በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የ“F” ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ፣ የኢትዮጵያ አትሌቶች አስደናቂ ብቃት በማሳየት ውድድሩን በድል አጠናቀዋል። በሩሲያ ዋና ከተማ በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፥ በአራት የተለያዩ የርቀት ዓይነቶችም የወርቅ ሜዳሊያዎችን ማሸነፍ ችለዋል። በሴቶች የ1500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም ርቀቱን በ3:58.59 በሆነ ፈጣን ሰዓት በማጠናቀቅ አንደኛ ወጥታለች። አትሌት ሳሮን በርሄ በ4:01.96 ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። በዚሁ ውድድር ላይ አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ፣ እንዲሁም አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሴቶች የ10000 ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በ32:23.54 አንደኛ በመሆን ስታሸንፍ፣ አትሌት ቤተልሔም ኦላና በ32:25.57 ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። ሌሎቹ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታደለ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል። በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ውድድር፣ ብርቱ ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ርቀቱን በ9:36.20 በማጠናቀቅ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በሴቶች 800 ሜትር ውድድር አትሌት ሀብታም ገበየሁ በ2:02.53 በሆነ ሰዓት 6ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በወንዶች የ10,000 ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ እጅግ ግሩም ውጤት አስመዝግቧል። አትሌት እዮብ ርቀቱን በ27:55.75 በማጠናቀቅ ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቋል። በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ በ28:16.57 ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቅ ችሏል። በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል ውድድር አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ ርቀቱን በ8:35.32 አንደኛ በመሆን በበላይነት አሸንፏል። አትሌት ሂርኮ ኃይሉ በበኩሉ ርቀቱን በ8:38.24 በማጠናቀቅ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። የ2026 ዳይመንድ ሊግ አራተኛ መዳረሻ በሆነው የሮሙ የሴቶች 5000 ሜትር ውድድር፣ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ ሰባተኛ ያለውን ደረጃ በሙሉ በመቆጣጠር በበላይነት አጠናቀዋል። በውድድሩም አትሌት ልቅና አምባው በ14:18.41 የወቅቱን የዓለም ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ የባለድልነት ዘውዱን ደፍታለች። አትሌት ልቅና አምባው የግሏን ምርጥ ሰዓት ከዓምስት ሰከንድ በላይ ማሻሻል የቻለች ሲሆን፥ የወቅቱ የርቀቱ ፈጣን በሆነው 14:18.41 ሰዓት ውድድሩን አሸንፋለች። ይህች አትሌት ቀደም ሲል በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ የሚታወስ ነው። በዚሁ የሮም ውድድር አትሌት አለሚቱ ባወቀ በ14:18.54 ሁለተኛ እንዲሁም አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ በ14:18.94 ሶስተኛ በመሆን ውድድሩን ማጠናቀቃቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል።
በምስራቅ ወለጋ ዞን በመኽር እርሻ 718 ሺህ ሄክታር መሬት ይለማል
Jun 6, 2026 76
ነቀምቴ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ወለጋ ዞን በመኽር እርሻ 718 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች እንደሚለማ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደረጄ ነገሰ እንደገለጹት፤ በመኽር እርሻ 718 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት ከ24 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል። ለዚህም ለአርሶ አደሩ አስፈላጊ የግብርና ግብዓቶችን በማቅረብ፣ ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። አሁን ላይ ያለው የዝናብ ሁኔታ ለግብርና ሥራው እጅግ አመቺ በመሆኑ፣ አርሶ አደሩ የተሻለ ምርት ለማግኘት በንቃት እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ኃላፊው ጠቅሰዋል። በመኽር እርሻው ከታቀደው መሬት ውስጥ እስካሁን 272 ሺህ 402 ሄክታሩ በዘር መሸፈኑን አቶ ደረጄ ገልጸዋል። ከግብዓት አንጻርም 473 ሺህ 379 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ቀርቧል ብለዋል። ዞኑ በበቆሎ ምርት የሚታወቅ በመሆኑ ልዩ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን፣ እስካሁን 255 ሺህ 92 ኩንታል የምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ተደርጓል ነው ያሉት። የምስራቅ ወለጋ ዞን የጉቶ ጊዳ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ሙላቱ በበኩላቸው፤ በወረዳው 64 ሺህ 139 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን 30 ሺህ 568 ሄክታሩ መልማቱን ተናግረዋል። በወረዳው ዘንድሮ ግብዓት በወቅቱ በመቅረቡ ምንም ዓይነት የእጥረት ስጋት እንደሌለ የጠቆሙት ኃላፊው፤ እስካሁን 47 ሺህ 166 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እና 5 ሺህ 124 ኩንታል ምርጥ ዘር መሰራጨቱን አስረድተዋል። የጉቶ ጊዳ ወረዳ አርሶ አደር አብዲሳ ቀናቴ፤ ማሳቸውን በክላስተር በማረስ በበቆሎ ዘር ለመሸፈን እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፤ ዘንድሮ የተሻለ ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ሌላኛው አርሶ አደር አቶ ተስፋ ይማም በበኩላቸው፤ በመኽር ወቅቱ 14 ሄክታር መሬት በበቆሎ ሰብል ለመሸፈን እያረሱ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ያገኘነውን የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በአግባቡ በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት እየተጋሁ ነው ብለዋል።
825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አድርገዋል
Jun 6, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን 825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎ በስኬት መጠናቀቁን አስታውሰዋል። በምርጫው ዕለት ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ተጀምሮ የነበረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት፣ እስከ ምሽቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ ተራዝሞ መጠናቀቁ ይታወቃል። ከምርጫው ማግስት ጀምሮ ጊዜያዊ ውጤቶች በየምርጫ ጣቢያዎቹ ሲለጠፉ መቆየታቸውን የገለጹት ሰብሳቢዋ፤ የየጣቢያዎቹ ውጤቶች ምስጢራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ወደ የምርጫ ክልሎቹ እንዲደርሱ መደረጉንና የማዳመር ሥራው ሲከናወን መቆየቱን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ቦርዱ ምርጫ ባካሄደባቸው አጠቃላይ 1 ሺህ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል፣ 825ቱ የማዳመር ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው ጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርገዋል ብለዋል። የማዳመር ስራን በመስራት ላይ ያሉ ቀሪ የምርጫ ክልሎች መኖራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ እነዚህ ቀሪ የምርጫ ክልሎች ሂደቱን በጥቂት ቀናት ውስጥ አጠናቀው ውጤት ይፋ እንደሚያደርጉ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ አረጋግጠዋል።
የሚታይ
825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አድርገዋል
Jun 6, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን 825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎ በስኬት መጠናቀቁን አስታውሰዋል። በምርጫው ዕለት ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ተጀምሮ የነበረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት፣ እስከ ምሽቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ ተራዝሞ መጠናቀቁ ይታወቃል። ከምርጫው ማግስት ጀምሮ ጊዜያዊ ውጤቶች በየምርጫ ጣቢያዎቹ ሲለጠፉ መቆየታቸውን የገለጹት ሰብሳቢዋ፤ የየጣቢያዎቹ ውጤቶች ምስጢራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ወደ የምርጫ ክልሎቹ እንዲደርሱ መደረጉንና የማዳመር ሥራው ሲከናወን መቆየቱን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ቦርዱ ምርጫ ባካሄደባቸው አጠቃላይ 1 ሺህ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል፣ 825ቱ የማዳመር ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው ጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርገዋል ብለዋል። የማዳመር ስራን በመስራት ላይ ያሉ ቀሪ የምርጫ ክልሎች መኖራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ እነዚህ ቀሪ የምርጫ ክልሎች ሂደቱን በጥቂት ቀናት ውስጥ አጠናቀው ውጤት ይፋ እንደሚያደርጉ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ አረጋግጠዋል።
የሚሊሻ ሃይሉ በልማትና የአካባቢውን ሰላም በማስከበር ረገድ በግንባር ቀደምትነት እየተሳተፈ ነው
Jun 6, 2026 120
ባህር ዳር፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሚሊሻ ሃይሉ ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት በልማትና የአካባቢውን ሰላም በማስከበር ተግባር ላይ በግንባር ቀደምትነት እየተሳተፈ መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን የምስረታ በዓል አከባበርና የእውቅና ፕሮግራም "የ30 ዓመታት የጀግንነት ታሪክ፤ ለዘላቂ ሰላም፣ ለሀገር ኩራት!" በሚል መሪ ሀሳብ በባህር ዳር ከተማ እየተከበረ ነው።   በበዓሉ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ በበዓሉ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለፁት፤ የሚሊሻ ሀይሉ ላለፉት 30 ዓመታት የህዝብና መንግስት አደራን በመወጣት አኩሪ ታሪክ ሰርቷል። ተግባሩን በማስቀጠልም የጠላቶችን ሴራ ለማክሸፍ ከፌደራልና ከክልሉ የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመቀናጀት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀትም ሰላምን በማስፈንና በልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ግንባር ቀደም ተግባር ማከናወኑን አንስተዋል። የሚሊሻ ሃይሉ የ30 ዓመታት ጉዞ በዓል ሲከበርም ለአገር፣ ለክልሉና ለአካባቢው ሰላም መረጋገጥ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በመዘከር መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ አክለዋል። የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ በበኩላቸው የክልሉ ሚሊሻ ኃይል ህዝባዊነትን በመላበስ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ ታሪክ የማይረሳው ጀግንነት ሲፈጽም መኖሩን ገልጸዋል።   በሰላም ጊዜ አርሶ አደር፣ በችግር ጊዜ ደግሞ ወታደር በመሆን የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር አስጠብቆ ለማቆየት ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። አሁን ላይ ተቋሙ በከፍተኛ ደረጃ ሪፎርም እያደረገ መሆኑን ጠቁመው ይህም ጠንካራ ተቋም በመገንባት ለሚሊሻ አባላት ተልዕኮን በላቀ ብቃት ለመፈጸም የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በዓሉን ስናክብርም ለሀገርና ለህዝብ ደህንነት ሲሉ መስዋዕትነት ለከፈሉ ጀግና የሚሊሻ አባላት ቤተሰቦች የሚደረገውን ሁለንተናዊ ድጋፍና እንክብካቤ አጠናክሮ ማስቀጠል ላይ በማተኮር ነው ብለዋል። በእለቱም በተቋሙ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩና የህዝብን ደህንነት ለማስጠበቅ መስዋዕትነት ለከፈሉ አባላትና ቤተሰቦቻቸው እውቅና የመስጠት መርሃ ግብር መካሄዱም ተመልክቷል።
ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጠናከር በትኩረት መስራቷን ትቀጥላለች
Jun 6, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማሳደግ የምታከናውናቸውን ተግባራት አጠናክራ እንደምትቀጥል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለፁ። የኢትዮጵያን ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ለኢዜአ እንዳሉት ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል ልማት በትኩረት እየሰራች ትገኛለች። ባለፉት ዓመታት የታላቁ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሶስት ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደስራ ማስገባት መቻሉን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት በስፋት መስራቷ በዘርፉ ተጠቃሽ ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ እንድትሆን ያስቻላት መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የምታመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ከታዳሽና ንፁህ ኃይል የሚገኝ መሆኑንም አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ተቋም ውስጥ በግንባር ቀደምነት እየሰራች መሆኗን አንስተው፤ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጎልበት የምታከናውነውን ተግባር አጠናክራ መቀጠሏንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ኃይል ከምታቀርብላቸው ከጅቡቲ፣ ሱዳንና ኬንያ በተጨማሪ ወደ ታንዛኒያ የኃይል ሽያጭ ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው ከሌሎች ሀገራት ጋርም በኃይል ለመተሳሰር ጥናት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለውጭ ሀገራት የምታቀርበው ከምታመነጨው ኃይል አስር በመቶ ያነሰ እንደሆነ በመግለጽ፤ የሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት የምታቀርበውን ኃይል በማቀናጀት በታዳሽ ኃይል ቀዳሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። ግዙፍ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። 16 የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮጀክቶችም በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ተቋሙ የኢትዮጵያን ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚሊሻ የሀገርና የሕዝብ ጥሪ ሲመጣ ማረሻውን ከቀዬው አኑሮ፣ መሣሪያውን በትከሻው አድርጎ ወደ ግንባር የሚተም የቁርጥ ቀን የሕሊና ወታደር ነው 
Jun 6, 2026 213
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ ሚሊሻ የሀገርና የሕዝብ ጥሪ ሲመጣ ማረሻውን ከቀዬው አኑሮ፣ መሣሪያውን በትከሻው አድርጎ ወደ ግንባር የሚተም የቁርጥ ቀን የሕሊና ወታደር ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን 30ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓል ላይ ተገኝተናል ብለዋል፡፡ የአማራ ክልል ሚሊሻ፣ ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ከፌደራልና ከክልል የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት፣ የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የሕዝባችንን ሰላም ለማስከበር ታላቅ መሥዋዕትነት የከፈለ ሕዝባዊ ኃይል ነው ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኃይል ልዩ የሚያደርገው ካለበት ማኅበረሰብ የወጣ፣ አብሮ የሚያርስና የሚያመርት፣ ሀገርና ክልል በገጠሟቸው ፈተናዎች ሁሉ ግንባር ቀደም በመሆን መሥዋዕትነትን በመክፈል ለሀገር ትልቅ አስተዋጽዖን አበርክቷል ብለዋል። ሀገራችንና ክልላችን ከተለዋዋጭና ውስብስብ የፀጥታ ተግዳሮቶች ጋር እየተጋፈጡ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ተቋማዊ አቅምን መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም፤ መንግሥታችን የሚሊሻውን ኃይል አደረጃጀት ዘመናዊ ለማድረግ፣ በዕውቀትና በሥልጠና ለማበልጸግ፣ በቴክኖሎጂ ለማዘመን እንዲሁም ትጥቅና አቅርቦቱን ለማሻሻል የጀመረውን ተቋማዊ የሪፎርም ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክትም ለሀገርና ለሕዝብ ሰላም ሲሉ ሕይወታቸውን ለሰጡ ጀግኖቻችን ታላቅ አክብሮትና ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አድርገዋል
Jun 6, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን 825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎ በስኬት መጠናቀቁን አስታውሰዋል። በምርጫው ዕለት ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ተጀምሮ የነበረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት፣ እስከ ምሽቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ ተራዝሞ መጠናቀቁ ይታወቃል። ከምርጫው ማግስት ጀምሮ ጊዜያዊ ውጤቶች በየምርጫ ጣቢያዎቹ ሲለጠፉ መቆየታቸውን የገለጹት ሰብሳቢዋ፤ የየጣቢያዎቹ ውጤቶች ምስጢራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ወደ የምርጫ ክልሎቹ እንዲደርሱ መደረጉንና የማዳመር ሥራው ሲከናወን መቆየቱን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ቦርዱ ምርጫ ባካሄደባቸው አጠቃላይ 1 ሺህ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል፣ 825ቱ የማዳመር ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው ጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርገዋል ብለዋል። የማዳመር ስራን በመስራት ላይ ያሉ ቀሪ የምርጫ ክልሎች መኖራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ እነዚህ ቀሪ የምርጫ ክልሎች ሂደቱን በጥቂት ቀናት ውስጥ አጠናቀው ውጤት ይፋ እንደሚያደርጉ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ አረጋግጠዋል።
የሚሊሻ ሃይሉ በልማትና የአካባቢውን ሰላም በማስከበር ረገድ በግንባር ቀደምትነት እየተሳተፈ ነው
Jun 6, 2026 120
ባህር ዳር፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሚሊሻ ሃይሉ ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት በልማትና የአካባቢውን ሰላም በማስከበር ተግባር ላይ በግንባር ቀደምትነት እየተሳተፈ መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን የምስረታ በዓል አከባበርና የእውቅና ፕሮግራም "የ30 ዓመታት የጀግንነት ታሪክ፤ ለዘላቂ ሰላም፣ ለሀገር ኩራት!" በሚል መሪ ሀሳብ በባህር ዳር ከተማ እየተከበረ ነው።   በበዓሉ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ በበዓሉ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለፁት፤ የሚሊሻ ሀይሉ ላለፉት 30 ዓመታት የህዝብና መንግስት አደራን በመወጣት አኩሪ ታሪክ ሰርቷል። ተግባሩን በማስቀጠልም የጠላቶችን ሴራ ለማክሸፍ ከፌደራልና ከክልሉ የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመቀናጀት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀትም ሰላምን በማስፈንና በልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ግንባር ቀደም ተግባር ማከናወኑን አንስተዋል። የሚሊሻ ሃይሉ የ30 ዓመታት ጉዞ በዓል ሲከበርም ለአገር፣ ለክልሉና ለአካባቢው ሰላም መረጋገጥ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በመዘከር መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ አክለዋል። የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ በበኩላቸው የክልሉ ሚሊሻ ኃይል ህዝባዊነትን በመላበስ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ ታሪክ የማይረሳው ጀግንነት ሲፈጽም መኖሩን ገልጸዋል።   በሰላም ጊዜ አርሶ አደር፣ በችግር ጊዜ ደግሞ ወታደር በመሆን የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር አስጠብቆ ለማቆየት ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። አሁን ላይ ተቋሙ በከፍተኛ ደረጃ ሪፎርም እያደረገ መሆኑን ጠቁመው ይህም ጠንካራ ተቋም በመገንባት ለሚሊሻ አባላት ተልዕኮን በላቀ ብቃት ለመፈጸም የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በዓሉን ስናክብርም ለሀገርና ለህዝብ ደህንነት ሲሉ መስዋዕትነት ለከፈሉ ጀግና የሚሊሻ አባላት ቤተሰቦች የሚደረገውን ሁለንተናዊ ድጋፍና እንክብካቤ አጠናክሮ ማስቀጠል ላይ በማተኮር ነው ብለዋል። በእለቱም በተቋሙ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩና የህዝብን ደህንነት ለማስጠበቅ መስዋዕትነት ለከፈሉ አባላትና ቤተሰቦቻቸው እውቅና የመስጠት መርሃ ግብር መካሄዱም ተመልክቷል።
ሚሊሻ የሀገርና የሕዝብ ጥሪ ሲመጣ ማረሻውን ከቀዬው አኑሮ፣ መሣሪያውን በትከሻው አድርጎ ወደ ግንባር የሚተም የቁርጥ ቀን የሕሊና ወታደር ነው 
Jun 6, 2026 213
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ ሚሊሻ የሀገርና የሕዝብ ጥሪ ሲመጣ ማረሻውን ከቀዬው አኑሮ፣ መሣሪያውን በትከሻው አድርጎ ወደ ግንባር የሚተም የቁርጥ ቀን የሕሊና ወታደር ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን 30ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓል ላይ ተገኝተናል ብለዋል፡፡ የአማራ ክልል ሚሊሻ፣ ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ከፌደራልና ከክልል የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት፣ የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የሕዝባችንን ሰላም ለማስከበር ታላቅ መሥዋዕትነት የከፈለ ሕዝባዊ ኃይል ነው ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኃይል ልዩ የሚያደርገው ካለበት ማኅበረሰብ የወጣ፣ አብሮ የሚያርስና የሚያመርት፣ ሀገርና ክልል በገጠሟቸው ፈተናዎች ሁሉ ግንባር ቀደም በመሆን መሥዋዕትነትን በመክፈል ለሀገር ትልቅ አስተዋጽዖን አበርክቷል ብለዋል። ሀገራችንና ክልላችን ከተለዋዋጭና ውስብስብ የፀጥታ ተግዳሮቶች ጋር እየተጋፈጡ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ተቋማዊ አቅምን መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም፤ መንግሥታችን የሚሊሻውን ኃይል አደረጃጀት ዘመናዊ ለማድረግ፣ በዕውቀትና በሥልጠና ለማበልጸግ፣ በቴክኖሎጂ ለማዘመን እንዲሁም ትጥቅና አቅርቦቱን ለማሻሻል የጀመረውን ተቋማዊ የሪፎርም ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክትም ለሀገርና ለሕዝብ ሰላም ሲሉ ሕይወታቸውን ለሰጡ ጀግኖቻችን ታላቅ አክብሮትና ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።
ህዝቡ ለሰላም ያለው ፅኑ አቋም የጽንፈኛ ቡድኖችን የተቀናጀ ምርጫ የማደናቀፍ ጥረት አክሽፏል 
Jun 6, 2026 305
ባህር ዳር፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝቡ ለሰላም ባለው ፅኑ አቋም የጽንፈኛ ቡድኖችን የተቀናጀ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ የማደናቀፍ ጥረት ሙሉ በሙሉ ማክሸፉን የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ ገለፁ። የሰላም ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በሸኔ የሽብር ቡድን የደረሰው ጥቃት የሚወገዝ መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ የበላይነት እንዲረጋገጥና የፀና መንግስትና ሀገር እንዲኖር ምርጫ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በዚህም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በታሪክ ሊጠቀስ በሚችል አግባብ ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ የተሳተፈበትን ሰላማዊ ምርጫ ማካሄድ ተችሏል ብለዋል። ምርጫው በሁሉም መለኪያዎች በውጭ ታዛቢዎች ጭምር የተረጋገጠ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ አግባብ ሊከናወን መቻሉን ገልፀዋል። ይሁን እንጂ ፅንፈኛ ቡድኖች ያለ የሌለ አቅማቸውን ተጠቅመው ምርጫውን ለማደናቀፍ ያደረጉትን የተቀናጀ ጥረት ሰላም ወዳዱ ህዝብ ሂደቱን ሰላማዊ በማድረግ ሴራቸውን አክሽፎታል ሲሉም ተናግረዋል። የባዕዳን ሴራ ተሸካሚ የሆኑ ፅንፈኛ ቡድኖች ከምርጫ በፊት ህዝብ ካርድ እንዳያወጣ፣ የድጋፍ ሰልፍ እንዳይወጣና በምርጫው ዕለት ድምፅ እንዳይሰጥ የተቀናጀ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም በሀገሩ የማይደራደረው የኢትዮጵያ ህዝብ ማስፈራሪያና ዛቻቸውን ብሎም የጥቃት ሙከራዎችን ተቋቁሞ ምርጫውን በማካሄድ ሴራቸውን በማክሸፍ የዲሞክራሲ የበላይነት እንዲረጋገጥ ማድረጉን አብራርተዋል። በምርጫው ሴራቸው የከሸፈባቸው ፅንፈኞች አሁንም ሌላ የጥፋት ካርድ በመምዘዝ የኢትዮጵያውያንን አንድነት፣ ህብረትና መተሳሰብ በማይመጥን መንገድ ሀገርን አደጋ ላይ የሚጥል ጥቃት መፈፀማቸውን ገልፀዋል። የሸኔ የሽብር ቡድን ከሰሞኑ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ጥቃት ማድረሱን አንስተው፤ ድርጊቱ በሁሉም ዘንድ መወገዝ ያለበትና ዳግም እንዳይከሰት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። ሆኖም አሳሳች ምስሎችን ጭምር በመጠቀም ችግሩን ለማባባስ በሴረኞች የተደረገው ጥረት በህዝቡ አስተዋይነት እና ሰላም ወዳድነት ሊከሽፍ መቻሉን ገልጸዋል። የህብረተሰቡን፣ የሃይማኖት ተቋማትን ብሎም በአማኞች መካከል ለዘመናት የተገነባውን የአብሮነት እሴት በማፍረስ ግጭት ለመቀስቀስ የተሄደበት ርቀት የሚወገዝ መሆኑን አንስተዋል። ጉዳዩ እንዳይራገብ ያደረጉ የመንፈሳዊ ማህበራት ወጣቶችን ያመሰገኑት ሚኒስትሩ በቀጣይ ችግሩን በማባባስ ሀገርና ህዝብን አደጋ ላይ ለመጣል የሚደረገውን ሴራ ሁሉም ሊከላከለው እንደሚገባም አሳስበዋል። ህዝቡ የጽንፈኞችን ምርጫን የማደናቀፍ ሴራ እንዳከሸፈው ሁሉ አብሮነትን በማጠናከር ሀገር የመገንባትና የማፅናት ተግባሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልም አስገንዝበዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ታላቅ ድል ነው - ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ
Jun 6, 2026 366
ባህር ዳር፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ በታላቅ ድል የሚታይ መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ አስታወቁ። ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረጉ በርካታ ሙከራዎችን በማክሸፍ ስኬታማ ምርጫ ማካሄድ መቻሉንም ገልጸዋል። ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረጉ የተለያዩ የጥፋት ሙከራዎች በሙሉ ከሽፈው የተሳካ ምርጫ መካሄዱን አንስተዋል። በታሪካቸው ከትጥቅ ትግል ውጪ የምርጫ ኮሮጆን የማያውቁ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የጥፋት አጀንዳ ተቀብለው በህዝብ ላይ ስጋትን ለመፍጠር ሁሌ የሚውተረተሩ አካላት ምርጫውን ለማደናቀፍ ሙከራ እድርገዋል ብለዋል። እነዚህ ተገዢ ባንዳዎች በመቀናጀት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይካሄድ ለማድረግ ከምርጫ በፊት፣ በምርጫ ወቅት እና ከምርጫ በኋላ የተለያዩ ሙከራዎችን አድርገዋ ሲሉ ገልጸዋል። ሆኖም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን በጋራ በመቆም ለጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳዩበት መድረክ መሆኑንም አክለዋል። በተለይም ጽንፈኛ ቡድኖች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ የተዛቡ መረጃዎችን ሲያሰራጩ መቆየታቸውን አስታውሰው፣ በምርጫው ሰሞንም የሽብር ድርጊቶችን ጭምር ለመፈጸም መሞከራቸውን አንስተዋል። ለአብነትም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኳስ እየተመለከቱ በነበሩ ተማሪዎች ላይ ቦምብ በመወርወር የአንድ ተማሪ ሕይወት እንዲያልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ በሌሎች ተማሪዎች ላይ ደግሞ የመቁሰል አደጋ አድርሰዋል ብለዋል። ጽንፈኞች የምርጫውን ዕለት ጨምሮ የተለያዩ ትንኮሳዎችን ያደረጉ ቢሆንም ሙከራው ሳይሳካ ቀርቷል ያሉት ሚኒስትሩ ይህ አልሳካ ያላቸው የጥፋት ኃይሎች በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በዜጎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ገልጸዋል። በጥቃቱም በጸጥታ አካላት፣ በቤተ እምነት፣ በመኖሪያ ቤቶች እና በመሠረተ ልማቶች ላይ ጉዳት ያደረሱ ሲሆን በተመሳሳይም በዞኑ ሀንቀሎ ዋቤ እና በሺርካ ወረዳዎች ተመሳሳይ ችግሮች መፍጠራቸውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ሁሉን አቀፍ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ሂደትም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አባቶች፣ ከኦሮሚያ ክልል አመራሮች እና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል ብለዋል። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ የተፈጠረውን ችግር ላልተገባ የፖለቲካ ጥቅም ለማዋል የሚደረገው ሙከራ ፍጹም ተቀባይነት እንደሌለውም ሚኒስትሩ አፅንኦት ሰጥተዋል። ሁኔታውን መነሻ በማድረግ የራስን የፖለቲካ ፍላጎት ለማሟላት የሚሯሯጡ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ አሳስበው፣ ጥፋተኛውን አካል በጋራ ማውገዝ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በአጠቃላይ፣ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍ በተለያዩ መንገዶች የሚገለጹ ሙከራዎች የነበሩ ቢሆንም፣ ምርጫው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል ብለዋል።
ተለዋዋጩን ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ በሳይንሳዊ መንገድ በመተንተን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ ነው
Jun 5, 2026 1309
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦ አሁናዊውንና ተለዋዋጩን ዓለም አቀፋዊ እንዲሁም ቀጣናዊ ሁኔታዎችን በሳይንሳዊ መንገድ በመተንተን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሰው ኃይሉን ለማብቃትና ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ በጀመረው አጠቃላይ የሪፎርም ሥራ መሠረት፣ ባለፉት ቀናት በነባራዊ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና ሲከታተሉ ለቆዩ አመራሮችና ሠራተኞች የሥልጠና ማጠናቀቂያ መርሃ ግብር አካሂዷል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በአሁኑ ወቅት የዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀያየሩ በመሆናቸው፣ ሂደቶቹን በሳይንሳዊ መንገድ መገምገም እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ተለዋዋጭ ሁኔታዎች በጥልቀት በመገንዘብ፣ ለፖሊሲ ውሳኔዎችና ስልታዊ እርምጃዎች የሚጠቅሙ ምክረ-ሐሳቦችን ለማቅረብ የዲፕሎማቶችን ሙያዊ ብቃት ማጎልበት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የተዘጋጀው ሥልጠና ተሳታፊዎቹ ወቅታዊ የዓለም ክስተቶችን በሙያዊ ዕይታ ለመተንተንና ክህሎታቸውን ለማሳደግ የላቀ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ በበኩላቸው፣ ሥልጠናው የተቋሙን የሰው ኃይል ክህሎትና ብቃት ለመገንባት የታለመው የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አካል መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ስትራቴጂክ ዕቅድ በተለያዩ እርከኖች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ በተሻለ ሁኔታ ለማስከበር የሚያስችላቸውን አቅም የሚፈጥር ነው። ስልጠናውን የሰጡት የቪየና ዓለም አቀፍ ጥናቶች ትምህርት ቤት ፕሮፌሰር ማርከስ ኮርንፕሮብስት (ዶ/ር) የምንኖርበት ዓለም በየወቅቱ ተለዋዋጭ እና ውስብስብ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ስለ ወቅታዊ ለውጦች፣ ስለ ዓለም አቀፉ ሥርዓት፣ ስለ መላው አፍሪካ እንዲሁም ስለ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ጠቃሚ ውይይቶች የተደረጉበት የሥልጠና ጊዜ መሆኑንም አስረድተዋል።
ፖለቲካ
825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አድርገዋል
Jun 6, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን 825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎ በስኬት መጠናቀቁን አስታውሰዋል። በምርጫው ዕለት ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ተጀምሮ የነበረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት፣ እስከ ምሽቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ ተራዝሞ መጠናቀቁ ይታወቃል። ከምርጫው ማግስት ጀምሮ ጊዜያዊ ውጤቶች በየምርጫ ጣቢያዎቹ ሲለጠፉ መቆየታቸውን የገለጹት ሰብሳቢዋ፤ የየጣቢያዎቹ ውጤቶች ምስጢራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ወደ የምርጫ ክልሎቹ እንዲደርሱ መደረጉንና የማዳመር ሥራው ሲከናወን መቆየቱን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ቦርዱ ምርጫ ባካሄደባቸው አጠቃላይ 1 ሺህ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል፣ 825ቱ የማዳመር ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው ጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርገዋል ብለዋል። የማዳመር ስራን በመስራት ላይ ያሉ ቀሪ የምርጫ ክልሎች መኖራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ እነዚህ ቀሪ የምርጫ ክልሎች ሂደቱን በጥቂት ቀናት ውስጥ አጠናቀው ውጤት ይፋ እንደሚያደርጉ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ አረጋግጠዋል።
የሚሊሻ ሃይሉ በልማትና የአካባቢውን ሰላም በማስከበር ረገድ በግንባር ቀደምትነት እየተሳተፈ ነው
Jun 6, 2026 120
ባህር ዳር፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሚሊሻ ሃይሉ ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት በልማትና የአካባቢውን ሰላም በማስከበር ተግባር ላይ በግንባር ቀደምትነት እየተሳተፈ መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን የምስረታ በዓል አከባበርና የእውቅና ፕሮግራም "የ30 ዓመታት የጀግንነት ታሪክ፤ ለዘላቂ ሰላም፣ ለሀገር ኩራት!" በሚል መሪ ሀሳብ በባህር ዳር ከተማ እየተከበረ ነው።   በበዓሉ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ በበዓሉ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለፁት፤ የሚሊሻ ሀይሉ ላለፉት 30 ዓመታት የህዝብና መንግስት አደራን በመወጣት አኩሪ ታሪክ ሰርቷል። ተግባሩን በማስቀጠልም የጠላቶችን ሴራ ለማክሸፍ ከፌደራልና ከክልሉ የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመቀናጀት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀትም ሰላምን በማስፈንና በልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ግንባር ቀደም ተግባር ማከናወኑን አንስተዋል። የሚሊሻ ሃይሉ የ30 ዓመታት ጉዞ በዓል ሲከበርም ለአገር፣ ለክልሉና ለአካባቢው ሰላም መረጋገጥ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በመዘከር መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ አክለዋል። የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ በበኩላቸው የክልሉ ሚሊሻ ኃይል ህዝባዊነትን በመላበስ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ ታሪክ የማይረሳው ጀግንነት ሲፈጽም መኖሩን ገልጸዋል።   በሰላም ጊዜ አርሶ አደር፣ በችግር ጊዜ ደግሞ ወታደር በመሆን የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር አስጠብቆ ለማቆየት ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። አሁን ላይ ተቋሙ በከፍተኛ ደረጃ ሪፎርም እያደረገ መሆኑን ጠቁመው ይህም ጠንካራ ተቋም በመገንባት ለሚሊሻ አባላት ተልዕኮን በላቀ ብቃት ለመፈጸም የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በዓሉን ስናክብርም ለሀገርና ለህዝብ ደህንነት ሲሉ መስዋዕትነት ለከፈሉ ጀግና የሚሊሻ አባላት ቤተሰቦች የሚደረገውን ሁለንተናዊ ድጋፍና እንክብካቤ አጠናክሮ ማስቀጠል ላይ በማተኮር ነው ብለዋል። በእለቱም በተቋሙ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩና የህዝብን ደህንነት ለማስጠበቅ መስዋዕትነት ለከፈሉ አባላትና ቤተሰቦቻቸው እውቅና የመስጠት መርሃ ግብር መካሄዱም ተመልክቷል።
ሚሊሻ የሀገርና የሕዝብ ጥሪ ሲመጣ ማረሻውን ከቀዬው አኑሮ፣ መሣሪያውን በትከሻው አድርጎ ወደ ግንባር የሚተም የቁርጥ ቀን የሕሊና ወታደር ነው 
Jun 6, 2026 213
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ ሚሊሻ የሀገርና የሕዝብ ጥሪ ሲመጣ ማረሻውን ከቀዬው አኑሮ፣ መሣሪያውን በትከሻው አድርጎ ወደ ግንባር የሚተም የቁርጥ ቀን የሕሊና ወታደር ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን 30ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓል ላይ ተገኝተናል ብለዋል፡፡ የአማራ ክልል ሚሊሻ፣ ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ከፌደራልና ከክልል የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት፣ የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የሕዝባችንን ሰላም ለማስከበር ታላቅ መሥዋዕትነት የከፈለ ሕዝባዊ ኃይል ነው ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኃይል ልዩ የሚያደርገው ካለበት ማኅበረሰብ የወጣ፣ አብሮ የሚያርስና የሚያመርት፣ ሀገርና ክልል በገጠሟቸው ፈተናዎች ሁሉ ግንባር ቀደም በመሆን መሥዋዕትነትን በመክፈል ለሀገር ትልቅ አስተዋጽዖን አበርክቷል ብለዋል። ሀገራችንና ክልላችን ከተለዋዋጭና ውስብስብ የፀጥታ ተግዳሮቶች ጋር እየተጋፈጡ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ተቋማዊ አቅምን መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም፤ መንግሥታችን የሚሊሻውን ኃይል አደረጃጀት ዘመናዊ ለማድረግ፣ በዕውቀትና በሥልጠና ለማበልጸግ፣ በቴክኖሎጂ ለማዘመን እንዲሁም ትጥቅና አቅርቦቱን ለማሻሻል የጀመረውን ተቋማዊ የሪፎርም ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክትም ለሀገርና ለሕዝብ ሰላም ሲሉ ሕይወታቸውን ለሰጡ ጀግኖቻችን ታላቅ አክብሮትና ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።
ህዝቡ ለሰላም ያለው ፅኑ አቋም የጽንፈኛ ቡድኖችን የተቀናጀ ምርጫ የማደናቀፍ ጥረት አክሽፏል 
Jun 6, 2026 305
ባህር ዳር፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝቡ ለሰላም ባለው ፅኑ አቋም የጽንፈኛ ቡድኖችን የተቀናጀ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ የማደናቀፍ ጥረት ሙሉ በሙሉ ማክሸፉን የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ ገለፁ። የሰላም ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በሸኔ የሽብር ቡድን የደረሰው ጥቃት የሚወገዝ መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ የበላይነት እንዲረጋገጥና የፀና መንግስትና ሀገር እንዲኖር ምርጫ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በዚህም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በታሪክ ሊጠቀስ በሚችል አግባብ ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ የተሳተፈበትን ሰላማዊ ምርጫ ማካሄድ ተችሏል ብለዋል። ምርጫው በሁሉም መለኪያዎች በውጭ ታዛቢዎች ጭምር የተረጋገጠ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ አግባብ ሊከናወን መቻሉን ገልፀዋል። ይሁን እንጂ ፅንፈኛ ቡድኖች ያለ የሌለ አቅማቸውን ተጠቅመው ምርጫውን ለማደናቀፍ ያደረጉትን የተቀናጀ ጥረት ሰላም ወዳዱ ህዝብ ሂደቱን ሰላማዊ በማድረግ ሴራቸውን አክሽፎታል ሲሉም ተናግረዋል። የባዕዳን ሴራ ተሸካሚ የሆኑ ፅንፈኛ ቡድኖች ከምርጫ በፊት ህዝብ ካርድ እንዳያወጣ፣ የድጋፍ ሰልፍ እንዳይወጣና በምርጫው ዕለት ድምፅ እንዳይሰጥ የተቀናጀ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም በሀገሩ የማይደራደረው የኢትዮጵያ ህዝብ ማስፈራሪያና ዛቻቸውን ብሎም የጥቃት ሙከራዎችን ተቋቁሞ ምርጫውን በማካሄድ ሴራቸውን በማክሸፍ የዲሞክራሲ የበላይነት እንዲረጋገጥ ማድረጉን አብራርተዋል። በምርጫው ሴራቸው የከሸፈባቸው ፅንፈኞች አሁንም ሌላ የጥፋት ካርድ በመምዘዝ የኢትዮጵያውያንን አንድነት፣ ህብረትና መተሳሰብ በማይመጥን መንገድ ሀገርን አደጋ ላይ የሚጥል ጥቃት መፈፀማቸውን ገልፀዋል። የሸኔ የሽብር ቡድን ከሰሞኑ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ጥቃት ማድረሱን አንስተው፤ ድርጊቱ በሁሉም ዘንድ መወገዝ ያለበትና ዳግም እንዳይከሰት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። ሆኖም አሳሳች ምስሎችን ጭምር በመጠቀም ችግሩን ለማባባስ በሴረኞች የተደረገው ጥረት በህዝቡ አስተዋይነት እና ሰላም ወዳድነት ሊከሽፍ መቻሉን ገልጸዋል። የህብረተሰቡን፣ የሃይማኖት ተቋማትን ብሎም በአማኞች መካከል ለዘመናት የተገነባውን የአብሮነት እሴት በማፍረስ ግጭት ለመቀስቀስ የተሄደበት ርቀት የሚወገዝ መሆኑን አንስተዋል። ጉዳዩ እንዳይራገብ ያደረጉ የመንፈሳዊ ማህበራት ወጣቶችን ያመሰገኑት ሚኒስትሩ በቀጣይ ችግሩን በማባባስ ሀገርና ህዝብን አደጋ ላይ ለመጣል የሚደረገውን ሴራ ሁሉም ሊከላከለው እንደሚገባም አሳስበዋል። ህዝቡ የጽንፈኞችን ምርጫን የማደናቀፍ ሴራ እንዳከሸፈው ሁሉ አብሮነትን በማጠናከር ሀገር የመገንባትና የማፅናት ተግባሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልም አስገንዝበዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ታላቅ ድል ነው - ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ
Jun 6, 2026 366
ባህር ዳር፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ በታላቅ ድል የሚታይ መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ አስታወቁ። ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረጉ በርካታ ሙከራዎችን በማክሸፍ ስኬታማ ምርጫ ማካሄድ መቻሉንም ገልጸዋል። ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረጉ የተለያዩ የጥፋት ሙከራዎች በሙሉ ከሽፈው የተሳካ ምርጫ መካሄዱን አንስተዋል። በታሪካቸው ከትጥቅ ትግል ውጪ የምርጫ ኮሮጆን የማያውቁ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የጥፋት አጀንዳ ተቀብለው በህዝብ ላይ ስጋትን ለመፍጠር ሁሌ የሚውተረተሩ አካላት ምርጫውን ለማደናቀፍ ሙከራ እድርገዋል ብለዋል። እነዚህ ተገዢ ባንዳዎች በመቀናጀት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይካሄድ ለማድረግ ከምርጫ በፊት፣ በምርጫ ወቅት እና ከምርጫ በኋላ የተለያዩ ሙከራዎችን አድርገዋ ሲሉ ገልጸዋል። ሆኖም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን በጋራ በመቆም ለጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳዩበት መድረክ መሆኑንም አክለዋል። በተለይም ጽንፈኛ ቡድኖች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ የተዛቡ መረጃዎችን ሲያሰራጩ መቆየታቸውን አስታውሰው፣ በምርጫው ሰሞንም የሽብር ድርጊቶችን ጭምር ለመፈጸም መሞከራቸውን አንስተዋል። ለአብነትም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኳስ እየተመለከቱ በነበሩ ተማሪዎች ላይ ቦምብ በመወርወር የአንድ ተማሪ ሕይወት እንዲያልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ በሌሎች ተማሪዎች ላይ ደግሞ የመቁሰል አደጋ አድርሰዋል ብለዋል። ጽንፈኞች የምርጫውን ዕለት ጨምሮ የተለያዩ ትንኮሳዎችን ያደረጉ ቢሆንም ሙከራው ሳይሳካ ቀርቷል ያሉት ሚኒስትሩ ይህ አልሳካ ያላቸው የጥፋት ኃይሎች በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በዜጎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ገልጸዋል። በጥቃቱም በጸጥታ አካላት፣ በቤተ እምነት፣ በመኖሪያ ቤቶች እና በመሠረተ ልማቶች ላይ ጉዳት ያደረሱ ሲሆን በተመሳሳይም በዞኑ ሀንቀሎ ዋቤ እና በሺርካ ወረዳዎች ተመሳሳይ ችግሮች መፍጠራቸውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ሁሉን አቀፍ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ሂደትም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አባቶች፣ ከኦሮሚያ ክልል አመራሮች እና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል ብለዋል። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ የተፈጠረውን ችግር ላልተገባ የፖለቲካ ጥቅም ለማዋል የሚደረገው ሙከራ ፍጹም ተቀባይነት እንደሌለውም ሚኒስትሩ አፅንኦት ሰጥተዋል። ሁኔታውን መነሻ በማድረግ የራስን የፖለቲካ ፍላጎት ለማሟላት የሚሯሯጡ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ አሳስበው፣ ጥፋተኛውን አካል በጋራ ማውገዝ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በአጠቃላይ፣ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍ በተለያዩ መንገዶች የሚገለጹ ሙከራዎች የነበሩ ቢሆንም፣ ምርጫው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል ብለዋል።
ተለዋዋጩን ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ በሳይንሳዊ መንገድ በመተንተን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ ነው
Jun 5, 2026 1309
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦ አሁናዊውንና ተለዋዋጩን ዓለም አቀፋዊ እንዲሁም ቀጣናዊ ሁኔታዎችን በሳይንሳዊ መንገድ በመተንተን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሰው ኃይሉን ለማብቃትና ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ በጀመረው አጠቃላይ የሪፎርም ሥራ መሠረት፣ ባለፉት ቀናት በነባራዊ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና ሲከታተሉ ለቆዩ አመራሮችና ሠራተኞች የሥልጠና ማጠናቀቂያ መርሃ ግብር አካሂዷል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በአሁኑ ወቅት የዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀያየሩ በመሆናቸው፣ ሂደቶቹን በሳይንሳዊ መንገድ መገምገም እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ተለዋዋጭ ሁኔታዎች በጥልቀት በመገንዘብ፣ ለፖሊሲ ውሳኔዎችና ስልታዊ እርምጃዎች የሚጠቅሙ ምክረ-ሐሳቦችን ለማቅረብ የዲፕሎማቶችን ሙያዊ ብቃት ማጎልበት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የተዘጋጀው ሥልጠና ተሳታፊዎቹ ወቅታዊ የዓለም ክስተቶችን በሙያዊ ዕይታ ለመተንተንና ክህሎታቸውን ለማሳደግ የላቀ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ በበኩላቸው፣ ሥልጠናው የተቋሙን የሰው ኃይል ክህሎትና ብቃት ለመገንባት የታለመው የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አካል መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ስትራቴጂክ ዕቅድ በተለያዩ እርከኖች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ በተሻለ ሁኔታ ለማስከበር የሚያስችላቸውን አቅም የሚፈጥር ነው። ስልጠናውን የሰጡት የቪየና ዓለም አቀፍ ጥናቶች ትምህርት ቤት ፕሮፌሰር ማርከስ ኮርንፕሮብስት (ዶ/ር) የምንኖርበት ዓለም በየወቅቱ ተለዋዋጭ እና ውስብስብ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ስለ ወቅታዊ ለውጦች፣ ስለ ዓለም አቀፉ ሥርዓት፣ ስለ መላው አፍሪካ እንዲሁም ስለ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ጠቃሚ ውይይቶች የተደረጉበት የሥልጠና ጊዜ መሆኑንም አስረድተዋል።
ማህበራዊ
በጋምቤላ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሂደት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል
Jun 6, 2026 93
ጋምቤላ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከአጋር አካላት ጋር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። በጋምቤላ ክልል ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በማስቀረት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን የሚገመግም መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሄዷል።   የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አርያት ኡጁሉ በመድረኩ እንደገለጹት፤ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በማስቀረት የሴቶችን የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ያስፈልጋል። በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ያለእድሜ ጋብቻ፣ በጋብቻ ላይ ጋብቻና ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በሴቶች ላይ የሚያደርሱት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት ከጎጂ ልማድ ጋር ተያይዞ ሴቶች ላይ ይደርስ የነበረውን ችግር በማስቀረት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ለውጦች መምጣታቸውን ተናግረዋል። በተለይም ቢሮው ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት ሴቶችን በእርሻ ልማት፣ በእርባታና ሌሎች የገቢ ማስገኛ ስራዎች በማሰማራት በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ረገድ አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል። የተገኙትን ለውጦች ይበልጥ ለማጠናከር አሁንም የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በቢሮው ግንዛቤ ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ግሩም ገብረኢየሱስ እንዳሉት፤ በክልሉ በሁሉም ቀበሌዎች የጎጂ ልማዳዊ ድርጊት አስወጋጅ ኮሚቴ በማቋቋም ያለእድሜ ጋብቻን ጨምሮ ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቀረት በትኩረት እየተሰራ ነው። ቢሮው ከጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቀረት የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። መድረኩ ላይ የክልሉ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን፣ በተከናወኑት ስራዎች ዙሪያ ሪፖርቶች ቀርበው ተገምግመዋል። በውይይት መድረኩ መጨረሻ አቅም ለሌላቸው ሴቶች የእርባታ ፍየሎችና የገንዘብ ድጋፍ ለተወካዮቻቸው ተበርክቷል።
ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ ነው
Jun 6, 2026 215
ሰመራ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጥናት እና ምርምር ተግባራት ማገዝ እንዳለባቸው የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዘካሪያስ ኤርኮላ (ዶ/ር) ተናገሩ። ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ከፌዴራል የህግና ፍትህ ኢንስቲቲዩት ጋር በመተባበር "ህገ-ወጥ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር፤ የህግ፣ ማህበራዊ እና ተቋማዊ አመለካከቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው አገር አቀፍ ሲምፖዚየም በሰመራ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት ዘካሪያስ ኤርኮላ (ዶ/ር)፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና ፍልሰትን ለመከላከል የሚደረገውን ሀገራዊ ጥረት በጥናትና ምርምር ማገዝ አለባቸው ብለዋል። የዚሁ አካል በሆነው በዚህ ሲምፖዚየም ላይ የቀረቡት የምርምር ፅሁፎች፣ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት የወጡ ህጎች አፈፃፀምና አተገባበር ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በውይይቱ የሚገኙት ግኝቶች ለፖሊሲ አውጪዎችና ለህግ ማሻሻያ ስራዎች በግብአትነት እንደሚያገለግሉም ገልጸዋል። ኢንስቲቲዩቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በህጎች አተገባበር ላይ የግንዛቤና የምርምር ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፤ ይህም ችግሩን በዘላቂነት ለማስወገድና የፖሊሲ ግብአቶችን ለማፍለቅ ትልቅ እገዛ አድርጓል ብለዋል። የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱረህማን ከድር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው ህገ-ወጥ ፍልሰትና የሰዎችን ዝውውር ለመግታት የድርሻውን እያበረከተ መሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም የአፋር ክልል ወደ የመንና ጅቡቲ ለሚደረገው ህገ-ወጥ ስደት እንደ መስመር የሚያገለግል በመሆኑ፣ ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ተቋማቸው በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህም ስኬታማነት ዩኒቨርሲቲው ለህብረተሰቡ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በማዘጋጀት፣ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠት እና ችግር ፈቺ ጥናቶችን በማካሄድ ረገድ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ አክለዋል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ አገር አቀፍ ሲምፖዚየም ላይ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ የህግና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ዲኖች፣ ተመራማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት ዘመኑን በሚመጥን አደረጃጀትና በላቀ ብቃት የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር እየጠበቀ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Jun 6, 2026 162
ድሬዳዋ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ዘመኑን በሚመጥን አደረጃጀትና በላቀ ብቃት የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር እየጠበቀ መሆኑን የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ። የሁርሶ ዕጩ መኮንኖች ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ያሰለጠናቸውን የ27ኛ ዙር ፅናት ኮርስ ዕጩ መኮንኖች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።   በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ሠራዊቱ ዘመኑን በሚመጥን አደረጃጀትና ብቃት በመታገዝ የሀገር ሉዓላዊነትና ክብርን እየጠበቀ መሆኑን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በየዘመናቱ ሉዓላዊነቷንና ክብሯን አስጠብቀው ያስረከቡን የጀግኖች ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ በዚህ ወቅትም ሠራዊቱ የላቀ ብቃቱን በተግባር እያስመሰከረ ይገኛል ብለዋል። ሠራዊቱ ከውጭ ጠላቶች ተልዕኮ ተቀብለው ሀገር የሚበድሉ ባንዳዎች እና ተላላኪዎችን የጥፋት ተልዕኮ እያመከነና ተከታተሎ ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ መሆኑንም ገልፀዋል።   የዛሬ ተመራቂዎችም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅም ላይ የሚቃጡ ጥቃቶችን በመመከት በጀግንነት መቆም እንዳለባቸው አሳስበዋል። ተመራቂዎቹ ያገኟቸውን ዘመናዊ ወታደራዊ ዕውቀት ካላቸው ተሞክሮ ጋር በማቀናጀት የሠራዊቱን ተልዕኮ አፈጻጸም ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል። የሁርሶ ዕጩ መኮንኖች ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አዛዥ ኮሎኔል ከድር ጫንጮ በበኩላቸው፤ ታሪካዊው ትምህርት ቤት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ክብር በታላቅ መስዋዕትነት የሚጠብቁ ጀግኖችን ማፍራቱን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። ተመራቂዎቹ በአካል ብቃት፣ በአመለካከት፣ በሥነ-ልቦና እና በሌሎች መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ በቂ ሥልጠና የወሰዱ በመሆናቸው፣ የትኛውንም ግዳጅ በብቃት መወጣት የሚችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። ተመራቂ መኮንኖቹ በበኩላቸው፤ በቀሰሙት ወታደራዊ ዕውቀትና ጥበብ ታግዘው የሀገርን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።   በማናቸውም ፈተና ውስጥ ሆነው የዜጎችን ደህንነት፣ የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ለመጠበቅም ቃል ገብተዋል። በመርሃ ግብሩ በመከላከያ ሚኒስቴር የትምህርትና ሥልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጄነራል ይመር መኮንን በሥልጠና ቆይታቸው የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዕጩ መኮንኖች ማዕረግ አልብሰዋል። በምረቃው የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ እንዲሁም ሌሎች ሀገር መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ፣ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን አስተዳዳሪ ወይዘሮ ሚስኪ መሐመድ እንዲሁም ኡጋዞችና አባገዳዎች ተገኝተዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳያችንን ባጠረ ጊዜ መፈጸም አስችሎናል - ተገልጋዮች
Jun 6, 2026 131
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳያቸውን ባጠረ ጊዜ መፈጸም እንዳስቻላቸው በወላይታ ሶዶ መሶብ የአንድ ማዕከል ተገልጋዮች ተናገሩ። በወላይታ ሶዶ ለኢዜአ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ተገልጋዮች መካከል የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ለማውጣት ወደ ማዕከሉ የመጡት አቶ ተስፋዬ ዳና አገልግሎቱን በቅርበት በማግኘታቸው ጊዜ እና ገንዘብ እንደቆጠበላቸው ተናግረዋል። የአገልግሎት አሰጣጡ ከኪራይ ሰብሳቢነት የጸዳና ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረን መጉላላት ያስቀረ መሆኑን ጠቅሰዋል።   አገልግሎቱ ፓስፖርት ለማውጣት ወደ ሐዋሳ በመሄድ ለበርካታ ቀናት የነበረውን መዘግየት እንዳስቀረለት የተናገረው ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ ወጣት በላቸው ዘውዴ ነው። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በፍጥነት በመስተናገድ ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን መቀነስ በመቻሉ መደሰቱን ጠቅሶ አገልግሎቱ ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክቷል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኃላፊ እና የወላይታ ሶዶ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ደመላሽ ታደሰ በበኩላቸው በማዕከሉ 4 የፌዴራልና 5 የክልል ተቋማት 32 የተለያዩ አገልግሎቶችን እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት አራት ወራት ብቻ ከ5 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተገልጋዮች አገልግሎት መስጠት መቻሉን ጠቁመዋል። በቀጣይ አገልግሎቱን ይበልጥ በማሻሻል የህዝብ ቅ
ኢኮኖሚ
በምስራቅ ወለጋ ዞን በመኽር እርሻ 718 ሺህ ሄክታር መሬት ይለማል
Jun 6, 2026 76
ነቀምቴ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ወለጋ ዞን በመኽር እርሻ 718 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች እንደሚለማ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደረጄ ነገሰ እንደገለጹት፤ በመኽር እርሻ 718 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት ከ24 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል። ለዚህም ለአርሶ አደሩ አስፈላጊ የግብርና ግብዓቶችን በማቅረብ፣ ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። አሁን ላይ ያለው የዝናብ ሁኔታ ለግብርና ሥራው እጅግ አመቺ በመሆኑ፣ አርሶ አደሩ የተሻለ ምርት ለማግኘት በንቃት እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ኃላፊው ጠቅሰዋል። በመኽር እርሻው ከታቀደው መሬት ውስጥ እስካሁን 272 ሺህ 402 ሄክታሩ በዘር መሸፈኑን አቶ ደረጄ ገልጸዋል። ከግብዓት አንጻርም 473 ሺህ 379 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ቀርቧል ብለዋል። ዞኑ በበቆሎ ምርት የሚታወቅ በመሆኑ ልዩ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን፣ እስካሁን 255 ሺህ 92 ኩንታል የምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ተደርጓል ነው ያሉት። የምስራቅ ወለጋ ዞን የጉቶ ጊዳ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ሙላቱ በበኩላቸው፤ በወረዳው 64 ሺህ 139 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን 30 ሺህ 568 ሄክታሩ መልማቱን ተናግረዋል። በወረዳው ዘንድሮ ግብዓት በወቅቱ በመቅረቡ ምንም ዓይነት የእጥረት ስጋት እንደሌለ የጠቆሙት ኃላፊው፤ እስካሁን 47 ሺህ 166 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እና 5 ሺህ 124 ኩንታል ምርጥ ዘር መሰራጨቱን አስረድተዋል። የጉቶ ጊዳ ወረዳ አርሶ አደር አብዲሳ ቀናቴ፤ ማሳቸውን በክላስተር በማረስ በበቆሎ ዘር ለመሸፈን እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፤ ዘንድሮ የተሻለ ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ሌላኛው አርሶ አደር አቶ ተስፋ ይማም በበኩላቸው፤ በመኽር ወቅቱ 14 ሄክታር መሬት በበቆሎ ሰብል ለመሸፈን እያረሱ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ያገኘነውን የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በአግባቡ በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት እየተጋሁ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጠናከር በትኩረት መስራቷን ትቀጥላለች
Jun 6, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማሳደግ የምታከናውናቸውን ተግባራት አጠናክራ እንደምትቀጥል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለፁ። የኢትዮጵያን ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ለኢዜአ እንዳሉት ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል ልማት በትኩረት እየሰራች ትገኛለች። ባለፉት ዓመታት የታላቁ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሶስት ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደስራ ማስገባት መቻሉን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት በስፋት መስራቷ በዘርፉ ተጠቃሽ ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ እንድትሆን ያስቻላት መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የምታመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ከታዳሽና ንፁህ ኃይል የሚገኝ መሆኑንም አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ተቋም ውስጥ በግንባር ቀደምነት እየሰራች መሆኗን አንስተው፤ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጎልበት የምታከናውነውን ተግባር አጠናክራ መቀጠሏንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ኃይል ከምታቀርብላቸው ከጅቡቲ፣ ሱዳንና ኬንያ በተጨማሪ ወደ ታንዛኒያ የኃይል ሽያጭ ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው ከሌሎች ሀገራት ጋርም በኃይል ለመተሳሰር ጥናት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለውጭ ሀገራት የምታቀርበው ከምታመነጨው ኃይል አስር በመቶ ያነሰ እንደሆነ በመግለጽ፤ የሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት የምታቀርበውን ኃይል በማቀናጀት በታዳሽ ኃይል ቀዳሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። ግዙፍ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። 16 የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮጀክቶችም በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ተቋሙ የኢትዮጵያን ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ ሳምንቱን ሙሉ ምርት የሚያቀርቡ የግብይት ማዕከላትን በማቋቋም ለማህበረሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርት እየቀረበ ነው 
Jun 6, 2026 129
ሆሳዕና፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ ለማቅረብ በተቋቋሙ የግብይት ማእከላት ከእሁድ እስከ እሁድ ምርቶች እየቀረቡ እንደሚገኝ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ምክትልና የግብይት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደስታ ዶሌቦ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በክልሉ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርቶችን በግብይት ማዕከላት በስፋት የማቅረብ ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል። በዚህም በክልሉ ከ140 በላይ ከእሁድ እስከ እሁድ ምርት የሚቀርብባቸው የግብይት ማዕከላትን በማቋቋም ለማህበረሰቡ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል።     ቢሮው በክልሉ 5 ከተሞች ዘመናዊ የግብይት ማዕከላት ማስገንባቱንና የወራቤ ከተማ ዘመናዊ የግብይት ማዕከል ለአገልግሎት ክፍት መደረጉን አስታውሰዋል። የግብይት ማዕከሉ አምራችና ሸማቹን ማህበረሰብ በቀጥታ በማገናኘት ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ማስቻሉን ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ነጋዴ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ሽታ መሀመድ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም የሚያመርቱትን ምርት በቀላሉ ለማህበረሰቡ ለማቅረብ የሚያስችል የግብይት ማዕከል ባለመኖሩ ገበያ ወዳለበት ስፍራ ይጓዙ እንደነበር ተናግረዋል።     በወራቤ ከተማ ተገንብቶ የተጠናቀቀው ዘመናዊ የግብይት ማዕከል የሚያመርቱትን ምርት ለማህበረሰቡ በቀላሉ ለማቅረብ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። በከተማው ስራ የጀመረው የግብይት ማዕከል የሚፈልጉትን ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስቻለ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የወራቤ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ሳድያ ጀማል ናቸው።     በከተማው ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው ዘመናዊ የግብይት ማዕከል ምርትን በጥራትና በፈለጉት ጊዜ ለማግኘት ማስቻሉን ተናግረዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በቅርቡ በወራቤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትንና ዘመናዊ የግብይት ማዕከልን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋቸው ይታወሳል።
በዞኑ አርሶ አደሮች የቆላ ፍራፍሬን በኩታ ገጠም በማልማት ተጠቃሚ እየሆኑ ነው
Jun 6, 2026 83
ገንዳ ውሃ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን የቆላ ፍራፍሬን በኩታ ገጠም በማልማት የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እያደገ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የመስኖና ውኃ አጠቃቀም ባለሙያ አቶ አስናቀው አራጋው እንደገለጹት፤ በዞኑ ለአካባቢው ሥነ-ምሕዳርና የአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ የሙዝ፣ የማንጎ፣ የፓፓያና የዘይቱን ፍራፍሬዎች በኩታ ገጠም ዘዴ እየለሙ ይገኛሉ። ይህንን ተግባር ይበልጥ በማስቀጠልም በመጪው ክረምት 200 ሄክታር መሬት በመተማና በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳዎች በኩታ ገጠም ለማልማት የጉድጓድ ቁፋሮ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ለተከላው የሚያስፈልጉ የቆላ ፍራፍሬ ችግኞችም በበጋው ወራት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የፍራፍሬ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ የባለሙያ ድጋፍና የተሻሻሉ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ፣ የሕዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም አቶ አስናቀው አስገንዝበዋል። ቀደም ሲል የተተከሉ የፍራፍሬ ምርቶች የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከመደገፍ ባለፈ፣ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ሀብት ማፍራት ማስቻላቸውንም ገልጸዋል። በዞኑ መተማ ወረዳ ወዲ ገምዞ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ሲሳይ ይመር በበኩላቸው፤ ለአካባቢው ሥነ-ምሕዳር ተስማሚ የሆኑ የቆላ ፍራፍሬዎችን በማልማት ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። ካለፉት ዓመታት ያገኙትን ልምድ በመጠቀምም በመጪው ክረምት ልማቱን ከአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ጋር በማስተሳሰር፣ የቆላ ፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሌላው የዞኑ የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ታርቆ አያሌው በበኩላቸው፤ ፍራፍሬን በተበታተነ ማሳ ከመትከል ይልቅ በኩታ ገጠም ማልማት ግብዓትን፣ ቴክኖሎጂንና ጉልበትን በጋራ በመጠቀም ምርታማ ለመሆን ያግዛል ብለዋል። ከዚህ በፊትም በሙዝ ልማት የተሳተፉ መሆናቸውን የገለጹት አርሶ አደሩ፣ አሁን ደግሞ በስፋት በማልማት የገቢ ምንጫቸውን ለማሳደግ እየሠሩ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል። በምዕራብ ጎንደር ዞን ባለፉት ዓመታት ከ1 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት በቆላ ፍራፍሬ የለማ መሆኑን ከዞኑ ግብርና መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል
Jun 5, 2026 580
ጎንደር፤ ግንቦት 28/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በኢኖቬሽን ዘርፍ የተቀረፁ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መተግበር የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዳዲስ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ለማበረታታት ያቋቋመው የቢዝነስና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ማእከል በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተመርቆ ስራ ጀምሯል።   ዩኒቨርሲቲው የማእከሉን ተልአኮና አላማ ማሳካት እንዲቻል ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የስምምነት ፊርማም ዛሬ አከናውኗል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ብለዋል። ኢኖቬሽንን ከማበረታታትና ከመደገፍ አንጻር ለፈጠራ ሃሳቦችና ስታርታፖች ምቹ ምህዳር ለመፍጠር ከምርምርና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቁርኝት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ነው ያሉት፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ችግር ፈቺ ምርምሮች ላይ ትኩረታቸውን በማድረግ የማህበረሰቡን ችግር በመፍታት በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ልማት ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎና አስተዋጽኦ ሊያደርጉ እንደሚገባም አመልክተዋል። ከዚህ አንጻር ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፋጠን ችግር ፈቺ ምርምሮች ላይ በማተኮር እያከናወናቸው የሚገኙ የምርምር ተግባራት ሞዴል መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ለማበረታታት ያቋቋመው የቢዝነስና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ማእከል የፈጠራ ሃሳቦች በልጽገው ወደ ተግባር የሚሸጋገሩበትን ምቹ የቴክኖሎጂ አውድ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡   የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው ማእከሉ የምርምር ሃሳብ ያላቸውን ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን በመቀበል ሃሳባቸውን ወደ መሬት የሚያወርዱበትን ምቹ የቴክኖሎጂ አውድ ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሰቲው ማእከሉን በቴክኖሎጂ፣ በባለሙያዎችና በዘመናዊ መሳሪያዎች በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገባ ማድረጉን ጠቁመው ስራ ፈጣሪዎች ምርምርና የፈጠራ ሃሳባቸው አድጎ ወደ ገበያ እንዲወጣ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡ ማእከሉ ችግር ፈቺ የምርምር ሃሳቦች ከመደርደሪያ ወርደው ወደ ኢንዱስትሪዎችና ካምፓኒዎች እንዲሸጋገሩ ብሎም የማህበረሰቡን ችግር መፍታት እንዲችሉ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር በመግለጽ። በማእከሉ የምረቃ ስነ ስርአት ላይ የአፍሪካ ልህቀት ማእከል ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብረሃን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።
በሐረሪ ክልል ከ38 ሺ 300 በላይ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደዋል- የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ
Jun 5, 2026 389
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ከ38 ሺ 300 በላይ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ጀማል ኢብራሂም ገለጹ። የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ ጀማል ኢብራሂም በሰጡት መግለጫ፤ የኮደርስ ሥልጠናው የዜጎችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት በማዳበር ረገድ እንደ አገር የተጀመረውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማሳለጥ ትልቅ እገዛ አለው ብለዋል። እስካሁን በኢኒሼቲቩ በተከናወነው ስራ በክልል ደረጃ ስልጠናውን ካጠናቀቁ ወጣቶች መካከል 27 ሺህ 574 የሚሆኑት የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውንም ጠቁመዋል። በመርሐ ግብሩ ፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አንድሮይድና ተያያዥነት ያላቸው ስልጠናዎች እየተሰጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ሥልጠናው ወጣቶችን የክህሎት ባለቤት ከማድረግ ባለፈ፣ ብቁ፣ ተወዳዳሪና ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል። ሥልጠናው ወጣቶችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ዕድሉን ያላገኙ ወጣቶች በቀጣይ ተመዝግበው እንዲሰለጥኑም ጥሪ አቅርበዋል።
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ለተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ስኬት የጎላ ሚና አላቸው
Jun 5, 2026 451
ጎንደር፤ ግንቦት 28/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ለተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ስኬት የጎላ ሚና እንዳላቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። ጎንደር ዩኒቨርሲቲ "በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ በጤና፣ በኑሮና በስነ ምህዳር ላይ ዘላቂ አቅምን መገንባት" በሚል መሪ ሀሳብ 32ኛውን ዓመታዊ የምርምር ጉባኤ እያካሄደ ነው።   ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በጉባኤው እንደገለጹት፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተገኘው ልምድና ተሞክሮ በመቀመር ለዲጂታል 2030 ግብ ስኬት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የላቀ አበርክቶ ሊኖራቸው ይገባል። በኢትዮጵያ እየተሰጠ ያለው የ5 ሚሊየን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወጣቱ ትውልድ የመጪው ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ እውቀት ባለቤት እንዲሆን አስቻይ ሁኔታን እንደሚፈጥርም አስረድተዋል። የዲጂታል መሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋት የተከናወኑ ተግባራት ለዲጂታል ኢኮኖሚው መጠናከር መሠረት መጣሉንም ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ ነው ብለዋል።   የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው በፈጣንና ተለዋዋጭ አለም ውስጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂን አስፈላጊነት በመረዳት ዩኒቨርሲቲው ምርምር ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በዚህም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ምርምርና የፈጠራ ስራዎችን በማበረታታት በዘርፉ ብቁ ተመራማሪዎችን ለማፍራት ትኩረት ተደርጓል ብለዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው ይህም ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ በይፋ ወደ ራስ ገዝነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት ያለመ መሆኑንም አመልክተዋል።   የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ የዘመኑ ትውልድ የወደፊቱን አለም መቀላቀል እንዲችል የዲጂታል ቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ባለቤት መሆን አለበት ብለዋል። በአለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አብዮት ኢትዮጵያ ተቀላቅላ መጓዝ ትችል ዘንድ ምሁራን በጥናትና ምርምር ማገዝ እንዳለባቸውም ገልጸዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ዓመታዊ የምርምር ጉባኤ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ተመራማሪዎች፣ መምህራንና ተማሪዎች በሚቀርቡ የምርምር ስራዎች ላይ እየተወያዩ ነው። በጉባኤው ላይ የተዘጋጀው የምርምርና የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽንም በዛሬው ዕለት ለእይታ ክፍት ተደርጓል።
ኢንስቲትዩቱ በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን ማስፈልፈል የሚያስችል ዘመናዊ የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል እያስገነባ ነው
Jun 5, 2026 404
ጋምቤላ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦የጋምቤላ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን ማስፈልፈል የሚያስችል የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል በማስገንባት ላይ መሆኑን አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ በጋምቤላ ከተማ ከ58 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ እያካሄደ ያለውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ሂደቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ ጎብኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ማዕከሉ የዶሮ እርባታውን ለማዘመንና ለማስፋት ዓይነተኛ ሚና ይኖረዋል።   በተለይም እንደ ሀገር ጤናማ የአመጋገብ ስርዓትን ለማጠናከር እየተተገበረ ያለውን የሌማት ትሩፋት መርሃግብር ስኬታማ ለማድረግ የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በመሆኑም የግንባታውን ሂደት በማፋጠን ወደ ስራ ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ለማዕከሉ ግንባታ መፋጠን የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ያደርጋልም ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሯ። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሪያል ጂንግ፤ ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተሻሻሉ የእንስሳትና የዕጽዋት ዝርያዎችን በማውጣት ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።   ኢንስቲትዩቱ እያስገነባ ያለው የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል የተሻሻሉ ዝርያዎች ለአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች ተደራሽ ለማድረግ ያለም መሆኑንም ተናግረዋል። በምርምር ኢንስቲትዩቱ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ አብዮት አለማየሁ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ የማዕከሉ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባ በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን የማስፈልፈል አቅም አለው። በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፍ ከ58 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለው ማዕከሉ አሁን ላይ ግንባታው ከ80 ከመቶ በላይ መድረሱን ገልጸዋል። የማዕከሉን 2ኛ ምዕራፍ ግንባታንም ለማስጀመር የጨረታ ሂደቱ መጠናቀቁንና በቅርቡ ስራው እንደሚጀመር አቶ አብዮት ገልጸዋል።
ስፖርት
በሮም እና ሞስኮ የደመቁት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች
Jun 6, 2026 76
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሮምና በሞስኮ በተካሄዱ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ድል አስመዝግበዋል። የዘንድሮው የዝናሜንስኪ ሜሞሪያል አትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ደማቅ ድል የተመዘገበበት መድረክ ሆኗል። በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የ“F” ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ፣ የኢትዮጵያ አትሌቶች አስደናቂ ብቃት በማሳየት ውድድሩን በድል አጠናቀዋል። በሩሲያ ዋና ከተማ በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፥ በአራት የተለያዩ የርቀት ዓይነቶችም የወርቅ ሜዳሊያዎችን ማሸነፍ ችለዋል። በሴቶች የ1500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም ርቀቱን በ3:58.59 በሆነ ፈጣን ሰዓት በማጠናቀቅ አንደኛ ወጥታለች። አትሌት ሳሮን በርሄ በ4:01.96 ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። በዚሁ ውድድር ላይ አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ፣ እንዲሁም አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሴቶች የ10000 ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በ32:23.54 አንደኛ በመሆን ስታሸንፍ፣ አትሌት ቤተልሔም ኦላና በ32:25.57 ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። ሌሎቹ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታደለ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል። በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ውድድር፣ ብርቱ ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ርቀቱን በ9:36.20 በማጠናቀቅ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በሴቶች 800 ሜትር ውድድር አትሌት ሀብታም ገበየሁ በ2:02.53 በሆነ ሰዓት 6ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በወንዶች የ10,000 ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ እጅግ ግሩም ውጤት አስመዝግቧል። አትሌት እዮብ ርቀቱን በ27:55.75 በማጠናቀቅ ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቋል። በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ በ28:16.57 ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቅ ችሏል። በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል ውድድር አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ ርቀቱን በ8:35.32 አንደኛ በመሆን በበላይነት አሸንፏል። አትሌት ሂርኮ ኃይሉ በበኩሉ ርቀቱን በ8:38.24 በማጠናቀቅ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። የ2026 ዳይመንድ ሊግ አራተኛ መዳረሻ በሆነው የሮሙ የሴቶች 5000 ሜትር ውድድር፣ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ ሰባተኛ ያለውን ደረጃ በሙሉ በመቆጣጠር በበላይነት አጠናቀዋል። በውድድሩም አትሌት ልቅና አምባው በ14:18.41 የወቅቱን የዓለም ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ የባለድልነት ዘውዱን ደፍታለች። አትሌት ልቅና አምባው የግሏን ምርጥ ሰዓት ከዓምስት ሰከንድ በላይ ማሻሻል የቻለች ሲሆን፥ የወቅቱ የርቀቱ ፈጣን በሆነው 14:18.41 ሰዓት ውድድሩን አሸንፋለች። ይህች አትሌት ቀደም ሲል በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ የሚታወስ ነው። በዚሁ የሮም ውድድር አትሌት አለሚቱ ባወቀ በ14:18.54 ሁለተኛ እንዲሁም አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ በ14:18.94 ሶስተኛ በመሆን ውድድሩን ማጠናቀቃቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር ነገ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Jun 6, 2026 272
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር ነገ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ውድድሩን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። መነሻው እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድር ላይ በወንዶች 455፣ በሴቶች ደግሞ 183 በድምሩ 638 አትሌቶች እንደሚሳተፉ በመግለጫው ላይ ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን የውድድሩ ዋና አላማ በስዊድን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድሩ ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች መምረጥ እና ተተኪዎች ማፍራት ነው ብለዋል። የፌዴሬሽኑ ውድድር እና ተሳትፎ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ጊዜ አድነው በበኩላቸው በውድድሩ ላይ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ደረጃ ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶች የገንዘብ፣ የሜዳልያና የዋንጫ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው አመልክተዋል። የዘንድሮው ውድድር ተሳታፊዎች ብዛት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የ434 አትሌቶች ጭማሪ ማሳየቱን የፌዴሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ ከማላዊ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ታደርጋለች
Jun 6, 2026 308
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ አቻው ጋር ዛሬ ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታውን ያከናውናል። ጨዋታው ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም ይካሄዳል። አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ለወዳጅነት ጨዋታዎቹ ዝግጅት ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለ23 ተጫዋቾች ያደረጉ ሲሆን፣ ብሔራዊ ቡድኑ ከግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ዝግጅቱን በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ሲያደርግ ቆይቷል። ዋልያዎቹ ዛሬ ከሚያደርጉት የመጀመሪያ ጨዋታ በፊት የመጨረሻ ልምምዳቸውን ትናንት በድሬዳዋ ስታዲየም አከናውኗል። ሁሉም የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የ55 ዓመቱ ዚምባቡዌያዊ አሰልጣኝ ካሊስቶ ፓሱዋ ለጨዋታው ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ አድርገው ቡድኑ ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል። ነበልባሎቹ የመጨረሻ ልምምዳቸውን ትናንት በድሬዳዋ ስታዲየም አድርጓል። ኢትዮጵያ እና ማላዊ ከዚህ ቀደም በውድድር እና በወዳጅነት ጨዋታዎች 14 ጊዜ ተገናኝተዋል። ዋልያዎቹ አራት ጊዜ ድል ሲቀናቸው ማላዊ አምስት ጊዜ አሸንፋለች። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ኢትዮጵያ በጨዋታዎቹ ላይ 16 ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ማላዊ 14 ጎሎችን አስቆጥራለች:: ሁለቱ ሀገራት ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት እ.አ.አ በ2022 እና በ2023 በኮትዲቯር ለተካሄደው 34ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ባደረጉት የማጣሪያ ጨዋታ ነበር። ከሁለቱ የማጣሪያ ጨዋታዎች መካከል ማላዊ አንዱን ስታሸንፍ በቀሪው ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ኢትዮጵያ ማላዊን ለመጨረሻ ጊዜ ያሸነፈችው እ.አ.አ በ2021 በባህር ዳር ስታዲየም በተካሄደ የወዳጅነት ጨዋታ ሲሆን ብሔራዊ ቡድኑ በወቅቱ የ4 ለ 0 ድል አስመዝግቧል። እ.አ.አ 1983 ቡድኖቹ ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ማላዊ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 አሸንፋለች። ጨዋታው፣ እ.አ.አ በ1986 በሜክሲኮ ለተስተናገደው 13ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የተደረገ የአፍሪካ ዞን ማጣሪያ ነበር። ሁለቱ ሀገራት ዛሬ ለ15ኛ ጊዜ ይገናኛሉ። በፊፋ የደረጃ ሰንጠረዥ ኢትዮጵያ 144ኛ፣ ማላዊ ደግሞ 127ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። ብሔራዊ ቡድኖቹ ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታቸውን ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ ስታዲየም ያደርጋሉ። ዋልያዎቹ ጨዋታዎቻቸውን የሚያደርጉት፣ የፊፋ ዓለም አቀፍ የብሔራዊ ቡድኖች የጨዋታ ቀናትን (FIFA Window) በመጠቀም መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Jun 5, 2026 410
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦ 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር እሁድ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ውድድሩን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። መነሻው እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድር ላይ በወንዶች 455፣ በሴቶች ደግሞ 183 በድምሩ 638 አትሌቶች እንደሚሳተፉ በመግለጫው ላይ ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን የውድድሩ ዋና አላማ በስዊድን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች መምረጥ እና ተተኪዎች ማፍራት ነው ብለዋል። የፌዴሬሽኑ ውድድር እና ተሳትፎ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ጊዜ አድነው በበኩላቸው በውድድሩ ላይ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ደረጃ ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶች የገንዘብ፣ሜዳልያና የዋንጫ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው አመልክተዋል። የዘንድሮው ውድድር ተሳታፊዎች ብዛት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የ434 አትሌቶች ጭማሪ ማሳየቱን የፌዴሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።
አካባቢ ጥበቃ
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው ተግባራዊ የተደረጉ ፕሮጀክቶች ለአካባቢ ጥበቃ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
Jun 6, 2026 164
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ የወንዝ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማቶችን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው የተተገበሩ ፕሮጀክቶች ለአካባቢ ጥበቃ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ገለጸ። የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ53ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ ተከብሯል። ቀኑን ምክንያት በማድረግም ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ከተማ የተውጣጡ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የስራ ሀላፊዎች እና ባለሙያዎች ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ የተሰራውን የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቱ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ ክፍት መደረጉ ይታወሳል።   የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው የተተገበሩ ፕሮጀክቶች የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው። በአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰው፤ ይህም የአየር ብክለት መቀነስን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች እያስገኘ ነው ብለዋል። ይህም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲቸራት ያስቻለ መሆኑን በመጠቆም፤ ሥነ ምህዳርን በማሻሻል በኩል ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም አብራርተዋል። የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ፕሮጀክት አካባቢ ጥበቃን ውጤታማ እያደረጉ ካሉ ሥራዎች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመው፤ የእንጦጦ ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ለዚህ አይነተኛ ማሳያ ነው ብለዋል። በፕሮጀክቱ ሀገር በቀል ዛፎች መተከላቸውን ጠቅሰው፤ ሀገር በቀል የኮንሶ የአካባቢ ጥበቃ እውቀቶች አሻራ ያረፈበት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም አንስተዋል። መሰል የአካባቢ ጥበቃና ልማት ሥራዎች ኢትዮጵያ ተምሳሌታዊና ተጠቃሽ ሀገር እያደረጋት ነው ሲሉም ዋና ዳይሬክተሯ አመላከተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ እሸቱ ለማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የእግረኛ መንገዶች፣የሳይክልና አማራጭ መንገዶችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።   ይህም በተሽከርካሪዎች ወደ አየር የሚለቀቀውን በካይ ጋዝ እንዲቀንስ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል። ፕሮጀክቱ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ለውጤት በቅቷል ከዚህ በኋላ ፕሮጀክቱ በሚጠበቀው ደረጃ አገልግሎት እንዲሰጥ ሕዝቡ ሊንከባከበው ይገባል ብለዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ዶኤ (ዶ/ር)፤ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያዊያን አቅም በአጭር ጊዜ ተገንብቶ ለውጤት መብቃቱ የሚደነቅ ነው ብለዋል።   ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ላይ ላላት ቁርጠኝነት መሰል የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ምስክሮች ናቸው ያሉት ተወካዩ ተፈጥሮን ከዘመናዊነት ጋር አጣጥሞ መሄድ ያለውን ውጤት አመላካች ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር ያስችላል
Jun 5, 2026 678
አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር የሚያስችል መሆኑን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን እና መሠረተ-ልማት ዲቪዚዮን ዳይሬክተር ሮበርት ሊሲንጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን በሚያሳልጡ በትራንስፖርት፣ ኢንዱስትሪ፣ ኃይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂዎች እና በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ነው፡፡ በዚህም በየዓመቱ ለነዳጅ የሚወጣውን ወጪ መቀነስና በታዳሽ ኃይል የሚመራ የትራንስፖርት ሥርዓት መገንባት የሚያስችል ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂና የትግበራ ዕቅድ ይፋ አድርጋለች፡፡ በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ኢኖቬሽን እና መሠረተ-ልማት ዲቪዚዮን ዳይሬክተር ሮበርት ሊሲንጌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂ ከዓለም አቀፍ የህግ ማዕቀፎች ጋር የተናበበ ነው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባ ነዳጅ ጥገኛ በመሆናቸው ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጭ እንደሚዳረጉ ገልጸው፤ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂና የትግበራ ዕቅድ ወጭን ከመቀነስ ባሻገር ለአስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ዋስትና ይሆናል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እያደረገች ያለችው ሽግግር የአየር ብክለትን በመቀነስ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት አጋዥ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር እስከ 2030 አዲስ ከሚመዘገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል 30 በመቶ የሚሆኑትን በሀገር ውስጥ ለማምረትና ለመገጣጠም ማቀዷ በአፍሪካውያን መካከል ያለውን የንግድ ትስስር ያጠናክራል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መጀመር ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚደረገውን ሽግግር ያሳልጣል ያሉት ዳይሬክተሩ፥ በአህጉሪቱ ያለውን የንግድ እሴት ሰንሰለት እንደሚያቀላጥፍም ገልጸዋል፡፡
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ
Jun 3, 2026 1090
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዮት አስታወቀ። የኢትዮጵያ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል። እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል። የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል። በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ይሆናል። በመደበኛ ሁኔታ ወቅታዊው የክረምት ዝናብ ቀደም ብሎ በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ አጋማሽ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚጀምር ሲሆን፤ በሂደት እየተጠናከረ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ አካባቢዎች እንደሚስፋፋም ገልጿል። በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛውና በምስራቅ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ዝናቡ በመጠንም ሆነ በስርጭት የተሻለ እንደሚሆን ይጠበቃል ብሏል። የሚኖረው እርጥበት ለግብርና ስራ የማሳ ዝግጅት እና የመኸር ሰብሎችን ለመዝራት እንዲሁም ለበልግ ሰብል ተጠቃሚ አካባቢዎች መልካም አጋጣሚ እንደሚኖረው ጠቁሟል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የአገሪቱ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው የገጽምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው ይጠበቃል ብሏል። በዚህም በመካከለኛው እና ታችኛው አባይ፣ ላይኛው እና መካከለኛ ባሮ አኮቦ፣ ላይኛው ስምጥ ሸለቆ፣ ኦሞ ጊቤ፣ አዋሽ እንዲሁም ገናሌ ዳዋ ከመካከለኛ እስከ ከባድ የገጸ ምድር ውሃ ፍሰት ይኖራቸዋል ብሏል። በላይኛው አባይ፣ ኦጋዴን፣ መካከለኛው አዋሽ፣ ስምጥ ሸለቆ እና ኦሞ ጊቤ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸውም ገልጿል።  
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማ ማህበረሰብን ለመፍጠር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው
Jun 3, 2026 884
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማ ማህበረሰብን ከመፍጠር አኳያ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሸጋው ፈንታዬ ገለጹ። ማህበሩ እነዚህን ስራዎች የሚደግፉ የምርምር፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ምቹ የአየር ፀባይ ሁኔታ እና ንጹህ አካባቢዎችን ለማስፋፋት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ፣ በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄና ሌሎች መርሃ ግብሮች በተከናወኑ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ ነው።   የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሸጋው ፈንታዬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ጤናማ ማኅበረሰብን ለመፍጠር ለዜጎች ተስማሚ የሆነ የመኖሪያ አካባቢን መፍጠር ይጠይቃል። የደኖች ጭፍጨፋ እንዲሁም የአካባቢን ንጽህና አለመጠበቅ የዜጎች ጤና ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር አንስተዋል።   በኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት ተግባራዊ የተደረጉት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እንዲሁም የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ስራዎች የአካባቢ ጤናን በመጠበቅ ለማኅበረሰብ ጤና ጉልህ አስተዋጽኦ አላቸው ብለዋል። የአካባቢን ንጽህና መጠበቅ ዜጎችን ከተለያዩ በሽታዎች እንደሚጠብቅም አክለዋል። የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማኅበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ስራዎች ላይ ገንቢ ሚና በመጫወት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ማህበሩ እነዚህን ስራዎች የሚደግፉ የምርምር፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።   የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አለማየሁ ሀዲስ በበኩላቸው፤ የአየር ንብረት ለውጥ መዛባት እና የአካባቢ ንጽህናን አለመጠበቅ በዜጎች ጤና ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ለመከላከል የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን እና አካባቢን ንጹህ ለማድረግ የሚሰሩ ተግባራትን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራን የአካባቢን ጤና ለመጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን ሊያጠናክሩ ይገባል ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 4415
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 4818
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 3654
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 3562
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 2204
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 4290
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው።   መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው።   በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል።   ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር።‎ ‎በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።   የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል።   በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል።   የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።   በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው።   በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል።   ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡   የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል።   በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል።   የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ።   በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል።   ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።   ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል።   በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ።   በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል።   የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል።   የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።  
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 3885
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 4116
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል።   በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል።   በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል።   የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።      
ትንታኔዎች
በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ …
Jun 3, 2026 1587
በዮሐንስ ደርበው በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር ሞላወርቅ አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በዓለምም ሆነ በሀገራችን አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው የደም ግፊት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በቆይታቸውም፤ ለደም ግፊት አጋላጭ ስለሆኑ ምክንያቶችና ሊደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄም እንዲሁም ከመድሃኒት አወሳሰድ ጋር በተያያዘ ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አቅርበዋል። · የደም ግፊት ምንድን ነው? ደም በደም ሥሮቻችን ሲያልፍ፤ የሚለካው መጠን “የደም ግፊት” እንደሚባል ዶክተር ሞላወርቅ ያስረዳሉ። የላይኛው (ሲስቶሊክ ወይም ከፍተኛው) የደም ግፊት መጠን ልብ በምትኮማተርበት ጊዜ ደም ወደ ደም ሥር ሲረጭ የሚለካው መሆኑንም ይገልጻሉ። የታችኛው (ዲያስቶሊክ ወይም ዝቅተኛው) የደም ግፊት መጠን ደግሞ ልብ ደም ለመቀበል ለአፍታ ዕረፍት በምታገኝበት ጊዜ የሚከሰት የግፊት ደረጃ መሆኑንም ይገልጻሉ። · የደም ግፊት ደረጃዎች እና ማስጠንቀቂያቸው ዶክተር ሞላወርቅ እንደሚሉት፤ የጤናማ ሰው የደም የግፊት መጠን 120 በ 80 እና በታች መሆን ይኖርበታል። በሌላ በኩል ግን ይላሉ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 የታችኛው ደግሞ ከ80 በታች ከሆነ “ከፍ ያለ ወይም የጨመረ የደም ግፊት ደረጃ” ይባላል። የላይኛው ከ130 እስከ 139 ወይም የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከሆነ ደግሞ “ደረጃ አንድ የደም ግፊት” እንደሚባል ያስረዳሉ። የላይኛው ከ140 በላይ ሲሆን እና የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ ደግሞ “ደረጃ ሁለት የደም ግፊት” እንደሚባል ነው የሚገልጹት። በሌላ በኩል “የከፋ የደም ግፊት ደረጃ” የሚባል እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም የላይኛው ከ180 በላይ እና የታችኛው ከ120 በላይ ሲሆን ነው በማለት ያብራራሉ። · ለደም ግፊት መጨመር መንስዔዎቹ ምንድን ናቸው? በዋናነት ሁለት ዓይነት የደም ግፊት መኖሩን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ ከፍተኛ የደም ግፊት እና መንስዔው የሚታወቅ የደም ግፊት መሆኑን አስረድተዋል። በዋናነት ወይም በአብዛኛው ከ90 እስከ 95 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ደም ግፊት የሚባለው መሆኑን ገልጸው፤ በርካታ መንስዔዎች ሊኖሩት እንደሚችሉ ቢገመትም ሁሉም በውል እንደማይታወቁ ያነሳሉ። ከበርካታ መንስዔዎቹ መካከልም፤ በቤተሰብ የሚወረስ (ተላላፊ)፣ አካባቢያዊ ምክንያቶች እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ የሚሉት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። የአኗኗር ዘይቤ ሲባልም፤ የአመጋገብ ሥርዓት በተለይም ጨው የበዛበት ምግብ፣ ክብደት መጨመር፣ አካባቢያዊ ሁኔታዎች (አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ)፣ የስኳር ታማሚ መሆን የሚሉት ይጠቀሳሉ ይላሉ። · ለደም ግፊት በተለይም እነማን ተጋላጭ ናቸው? ዕድሜ በጨመረ ቁጥር የደም ግፊት የመከሰት ዕድሉም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በዚህም መሠረት ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ይናገራሉ። እንዲም በቤተሰብ የደም ግፊት ኬዝ ያለባቸው ሰዎች፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒክ ግሩፕ) ለምሳሌ፡- በጥቁሮች (አፍሪካውያን)፣ በኤስያውያን፣ በደቡብ ኤስያውያን ላይ ከፍተኛ የደም ግፊት ሊከሰት እንደሚችል ይገልጻሉ። እንደ ዶክተር ሞላወርቅ ማብራሪያ፤ በአጠቃላይ አጋላጭ ምክንያቶች በሁለት ተከፍለው ሊታዩ ይችላሉ። አንደኛው፡- ልንከላከላቸው (ልንቀንሳቸው) የምንችላቸው መሆናቸውን በመግለጽ ይህም የአመጋገብ ሥርዓትን ማስተካከል፣ ክብደት መቀነስ፣ አልኮልና ሲጋራ ማቆም እና መሰል መሆናቸውን አብራርተዋል። ሁለተኛው፡- ልንከላከላቸው የማንችላቸው መሆናቸውን ገልጸው ይህም፤ የዕድሜ መጨመር፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒሲቲ) እና በቤተሰብ የሚተላለፍ የሚሉትን ጠቅሰዋል። · የደም ግፊትን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? የደም ግፊ ከተከሰተ መቆጣጠር እንጅ ማዳን እንደማይቻል ገልጸው፤ ከላይ እንደተጠቀሰው አስቀድሞ መከላከል ወይም ማዘግየት የሚቻል እና መከላከል የማይቻል የደም ግፊት ደረጃ መኖሩን አስረድተዋል። · የደም ግፊት በውል የሚታወቅ ምልክት አለው? የደም ግፊት ሲከሰት ምልክት እንደሌለው በማንሳት፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ “ዝምተኛው ገዳይ” እስከመባል መድረሱን ዶክተር ሞላወርቅ ያነሳሉ። ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ግን፤ በአንድ ወይም በሁለት የሰውነት አካል ላይ ችግር ሊደርስ እንደሚችል ከዚህም ሲያልፍ እስከ ሞት እንደሚያደርስ ይጠቅሳሉ። በተያያዘም፤ የራስ ምታት፣ የዐይን ብዥ ብዥ ማለት፣ ትንፋሽ ማጠር፣ የድካም ስሜት፣ አንገት የመያዝ ዓይነት ስሜቶች የደም ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ሊስተዋሉ የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል። አክለውም፤ በአብዛኛው በሕብረተሰቡ ላይ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርስና ድንገት በጨመረ ጊዜ፤ ለሞት፣ ለአደጋ፣ ለልብ ድካም፣ አጣዳፊ ለሆነ የልብ ህመም፣ በጭንቅላት ላይ የደም መፍሰስ፣ የኩላሊት ድክመት፣ በደም ሥሮች በአግባቡ ደም እንዳይተላለፍ ማድረግ፣ ለዐይነ ስውርነት መዳረግን ጨምሮ መሰል ጉዳቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝበዋል። · መድኃኒት አወሳሰድ ላይ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ ዶክተር ሞላወርቅ እንደገለጹት፤ አንድ ሰው ደም ግፊት እንዳለበት ከተነገረው በኋላ ሕክምናውም እንደ ደም ግፊቱ ደረጃ ይለያያል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 ከሆነ “የጨመረ ግፊት” ይባላል፤ እዚህ ላይ ሰውየው ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አመጋገቡን እንዲያስተካክል፣ ስፖርት እንዲሠራ፣ ክብደት እንዲቀንስ፣ ሱስ (ሲጋራ፣ አልኮል) እንዲቀንስ ክትትል ይደረጋል ብለዋል። ስለዚህ መድኃኒት ሳይጀምር የአኗኗር ዘይቤን በማስተካከል የደም ግፊቱን ሊቀንሰው (ሊቆጣጠረው) ይችላል ማለት ነው ሲሉም ይገልጻሉ። “ደረጃ አንድ ግፊት” የሚለው ላይ ከደረሱ ግን ሕክምና የሚጀምሩም የማይጀምሩም እንዳሉ ተናግረዋል። ይህም ማለት የላይኛው ከ130 እስከ 139 የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከደረሰ ሕክምና የሚጀምሩት የስኳር ህመም ያለባቸው፣ የስትሮክ ህመም ያለባቸው፣ ከልብና ደም ሥር የተገናኙ ህመሞች ያሉባቸው ከሆኑ ቢያንስ አንድ የግፊት መድኃኒት መጀመርና ክትትል ማድረግ አለባቸው ይላሉ። በሌላ በኩል ግን ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ ሰዎች “ደረጃ ሁለት ግፊት” ላይ ከደረሱ (የላይኛው ከ140 የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ) ሁሉም መድኃኒት መጀመር እንዳለባቸው በአጽንዖት ገልጸዋል። የሚጀምሩት መድኃኒትም አሁን ባለው በተሻሻለው የሕክምና ዘይቤ ሁለት መድኃኒቶች የሚጀምሩበት ሁኔታ እንዳለ ነው የሚያስረዱት። የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ግን ለሁሉም የግፊት ዓይነቶች መሠረት (የሚመከር) መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ መድኃኒት ጀምሬያለሁ ብሎ የአኗኗር ዘይቤው ላይ ቸልተኝነት ሊኖር እንደማይገባም ነው የሚመከሩት። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከግፊት ጋር በተያያዘ ወደ ሆስፒታል መጥተው የሚታከሙ ታካሚዎች አብዛኞቹ፤ ጀምረው ያቋረጡ፣ ለመጀመር ፍላጎት የሌላቸው፣ ቅድመ ምርመራ ባለማድረግ ምክንያት ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ የተጎዱ ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። ስለዚህ የግፊት መድኃኒት ከተጀመረ ሊቋረጥ እንደማይችል አስጠንቅቀዋል። በየጊዜው ክትትል ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በሂደት እንደ ግፊቱ ሁኔታ መድኃኒቶች ሊቀነሱም ሊጨመሩም እንደሚችሉ አመላክተዋል። · የመስፋፋት ደረጃ የዓለም ጤና ድርጅት በ2024 ያወጣውን መረጃ ዋቢ አድርገው፤ 1/3ኛው የዓለም ሕዝቦች በደም ግፊት እንደሚጠቁ ዶክተር ሞላወርቅ አንስተዋል። ከእነዚህ መካከልም፤ 7 ነጥብ 6 ሚሊየን ገደማው በአንድም በሌላም ምክንያት ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ጠቁመዋል። አብዛኞቹ የደም ግፊት ታማሚዎች ቁጥር የሚመዘገበው ደግሞ በመካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ሀገራችንን ያካትታል ሲሉ ገልጸዋል። በሀገራችን ደረጃም ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ባይኖሩም ከግፊት ጋር በተያያዘ በ2001 ላይ በ35 ሳይቶች የተጠኑ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከ21 እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ በደም ግፊት የሚጠቃ ነው ይላሉ። በአብዛኛው ደግሞ ከተማ ላይ እንደሚበዛ ጠቁመው፤ በተለይም አዲስ አበባ ላይ እስከ 30 በመቶ እንደሚደርስ የጥናቶቹ ውጤቶች ማመላከታቸውን ተናግረዋል። አብዛኞቹ ኬዞች ደግሞ ዕድሜያቸው ከፍ ያለ፣ ክብደታቸው የጨመረ፣ አልኮል እና ሲጋራ የሚጠቀሙ እና የስኳር ህመም ያለባቸው ሰዎች ጋር የሚገናኙ መሆናቸውን አስረድተዋል። እንደ ዓለም አቀፍ ደረጃም ኬዙ ካለባቸው መካከል ግማሽ ያህሉ ግፊት እንዳለባቸው እንኳን እንደማያውቁ ነው የሚገልጹት። ለግፊት ሕክምና ትክክለኛ ክትትል አድርገው ግፊታቸውን በአግባቡ የሚቆጣጠሩት ከ 5 ሰዎች 1 መሆኑንም ጥናቶች ያሳያሉ ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ በሀገራችን በሕብረተሰቡ ዘንድ ለደም ግፊት መለካት ኬዙ ከተገኘም የሕክምና ክትትል የማድረግ ሁኔታዎች ዝቅተኛ መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ሕብረተሰቡ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከአካል ጉዳት እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል ተገንዝቦ፤ የደም ግፊቱን የመለካት ልምምዱን ሊያዳብር እንደሚገባ ዶክተር ሞላወርቅ መክረዋል። በሌላ በኩል እንደ ሀገራችን ባሉ ሆስፒታሎች በጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ ወይም መቋረጥ (ስትሮክ) ካለባቸው ሰዎች ከ70 እስከ 85 በመቶው ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ የሚከሰት መሆኑን ገልጸው፤ ድንገተኛ ግፊት መጨመር ከልብ እና ከደም ሥሮች ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዓለምም ሆነ እንደ ሀገር አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንደኛው ግፊት መሆኑንም አረጋግጠዋል። ስለዚህ የደም ግፊትን መለካት፣ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል፣ ከሱስ መራቅ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር ለጤናማ ሕይወት ከፍተኛ ሚና እንዳለው መክረዋል።  
 ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 4861
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 2605
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ‎ ‎​ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። ‎ ‎መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ‎ ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት
May 17, 2026 6159
በኢዜአ ዐይን …! በዮሐንስ ደርበው እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉን የሚሉ እሮሮዎች በተለያዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሲነሱ ቆይተዋል። በተለይም በአንዳንድ ተቋማት መንግሥታዊ አገልግሎት ለማግኘት እዚያም እዚህም መንከራተት፤ደግሞም ወረፋ በመጠበቅ መጉላላት ብሎም ለጊዜና ገንዘብ ወጪ መዳረግ ይስተዋላል የሚሉ ሐሳቦች ተስተጋብተዋል። ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ባሳለፍነው ሳምንት … መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል አሠራር በመንደፍ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ አስጀመረ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማዕከሉ አገልግሎት ባስጀመሩበት ወቅትም ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው ብለው ነበር። አሁን ላይም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ነው።መስፋፋቱም በማዕከላት ብዛት፣በአገልግሎት መስጫ መስኮቶች ቁጥር እና በአገልግሎት ዐይነቶች እየተገለጠ ነው። በዚህም በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት የተደራጁ ሲሆን ይህ አሃዝም ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እና ያለውን ፈጣን እድገት ያመላክታል። ጉዳዩ የዜጎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ማላቅ፤ ብልሹ አሠራርንም መቅረፍ ነውና መንግሥት በልዩ ትኩረት ይዞታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ አሥተዳደርና በሐረሪ ክልል ጉብኝት ባደረጉበት ወቅትም፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የምልከታቸው አካል ማድረጋቸው ለጉዳዩ የተሰጠውን ከፍያለ ትኩረት ያሳያል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሶብ የሞባይል አገልግሎትን በመረቁበት ወቅት ደግሞ፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ብለዋል። አክለውም፤በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች ዕርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል፤ ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፤ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ መሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል ማለቱም ይታወቃል። የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ደግሞ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ ያስቻለ ስኬት ተገኝቷል ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ የመንግሥት አገልግሎቶችም ዜጋ ተኮር፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አብራርተዋል። በዲጂታል 2030 የአገልግሎት አሰጣጥ አመላካች ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚጠቀሱ 50 ሀገራት መካከል አንዷ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ዜጎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በኦንላይን በየትኛውም ቦታ ሁሉንም አገልግሎቶች እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ ስለመሆኑም እንዲሁ። አገልገሎቱን ያገኙ አስተያየት ሰጭዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ እንግልትን ያስቀረ፣ ጊዜና ወጭን የቀነሰ ነውና ይስፋፋ፤ ተጠናክሮም ይቀጥል። #መሶብ_የአንድ_ማዕከል_አገልግሎት #የዜጎችን_እንግልትና_ብልሹአሠራርን_መቅረፍ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #በኢዜአ_ዐይን
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 11320
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 6416
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 12191
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 10667
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 74982
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 62141
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 42536
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 40107
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 31597
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 31036
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 30515
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 29837
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 74982
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 62141
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 42536
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 40107
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 2204
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 5455
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም