ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
አዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን ዝግጅት እያደረገ ነው
Oct 29, 2025 41
አዳማ ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- አዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን የቅድመ ዝግጅት ተግባር እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ለሚ ጉታ(ዶ/ር) ፤ ተቋሙ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ለሀገር እድገት በሚገባው ልክ አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ራስ ገዝ ለመሆን እየተዘጋጀ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ተከትሎ ራስ ገዝ ለመሆን የትምህርት ሚኒስቴር መስፈርቶችን ማሟላት በሚያስችል አግባብ ላይ እንደሆነ ተናግረዋል። ከዝግጅቱም ውስጥ የተቋማዊ ግምገማ ሠነድ፣ ስትራቴጂክ እቅድ፣ፖሊሲና መመሪያዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። ይህንንም ተከትሎ ዩኒቨርስቲው ራስ ገዝ (የአውቶኖመስ) የመሆን ጥያቄውን ለትምህርት ሚኒስቴር በይፋ ማቅረቡን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስታውቀዋል። በተለይ የመማር ማስተማር፣የምርምር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይም ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከነዚህ ስራዎች ውስጥ ባለፈው በጀት ዓመት የተጠናቀቀው የምርምር ፓርክ ግንባታን አንስተዋል። በዚህ የምርምር ፓርክ ውስጥ ለሚገኙ አምስት የልህቀት ማዕከላት 30 ቤተ ሙከራዎችን የማደራጀት ስራ ተጀምሯል ብለዋል። ይህ ፓርክ ከዩኒቨርሲቲው ባሻገር እንደ ሀገር በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ግዙፍ እና ልዩ የምርምር ማዕከል በመሆን የላቀ ፋይዳ እንደሚኖረው አስረድተዋል። በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው ዘመናዊ የዳታ ማዕከል፣የ10 ኪሎ ሜትር አስፋልት እና አራት ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መንገድና ሌሎችም ግንባታዎች እየተገባደዱ ይገኛሉ ብለዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1294/2015 በአብላጫ ደምፅ ማጽደቁ ይታወሳል። አዋጁ ለሀገር ዕድገት ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በምርምር የላቀ እውቀት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት የሚሰሩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ለመገንባት ያለመ ነው። ከዚህም ባለፈ ዩኒቨርሲቲዎቹ ሙያዊ ተልዕኳቸውን በላቀ ብቃት ተመራማሪዎችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ። የጥናትና ምርምር፣ የትምህርትና የማህበረሰባዊ ነጻ አገልግሎት የሚያከናውኑበትን የፋይናንስ ምንጭ መሰብሰብና ሀገራዊ ልማትን ማገዝ የሚችሉበትን ነጻ ምህዳር ለመፍጠር ትልቅ ዕገዛ እንዲኖረው ተደርጎ በውይይት ዳብሮ መዘጋጀቱን በወቅቱ ተጠቅሷል።
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Oct 29, 2025 35
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር በመሰረተ ልማት ያላትን ትስስር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላትም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስቴር ፒዬንግ ዴንግ ኩኦል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ልዑካን ቡድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን በተለይም በአቢዬ ግዛት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ገለጻ አድርጓል። ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አጠናቃ በስኬት በማስመረቋ ደስታቸውን በመግለጽ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት በህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ በመሳተፋቸውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በመሰረተ ልማት የበለጠ በመተሳሰር ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጎልበት ሊሰሩ እንደሚገባም መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን የተጠቀሙ አርሶ አደሮች ውጤታማ ሆነዋል
Oct 29, 2025 29
ጊምቢ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን ከግብርና ማዕከል የወጡ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን የተጠቀሙ አርሶ አደሮች ከልማቱ የተሻለ ገቢ በማግኘት ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በፍራፍሬ ልማት ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ከመንግስት ባገኙት የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን ተጠቅመው በማልማት ገቢ አግኝተው የተሻለ ኑሮ መምራት መጀመራቸውን ገልጸዋል። የተሻሻሉ ዝርያዎቹን ከተጠቀሙ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ የሆማ ወረዳ ነዋሪው አቶ ተካልኝ ኤፍሬም፣ ከዚህ በፊት በቡና ልማት ላይ ብቻ ጥገኛ ሆነው መቆየታቸውን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ ዝርያቸው የተሻሻሉ ፍራፍሬዎችን በመጠቀም በማልማታቸው ውጤታማ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። አቮካዶና ሙዝ በማልማት በዓመት እስከ 25 ሺህ ብር ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስተው በዚህም ህይወታቸውን በተሻለ መንገድ እየመሩ መሆኑን ተናግረዋል። የላሎ አሳቢ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር ገረመው ጅሬኛ በበኩላቸው ከግብርና ማዕከል የወጣ የተሻሻለ የሙዝ ዝርያን በማልማት ኢኮኖሚያቸው እያደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ ልማቱን በማጠናከር የሙዝ ዝርያዎችን በማባዛትና በማልማት ተጠቃሚነታቸውን የበለጠ ለማሳደግ ተግተው እንደሚሰሩም ጠቅሰዋል፡፡ በምዕራብ ወለጋ ዞን የግብርና ጽህፈት ቤት የፍራፍሬ ልማት ባለሙያ አቶ ጂብሪል መንጌ እንደገለጹት በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች የፍራፍሬ ልማት በሰፊው እየተካሄደ ነው። በእስካሁኑ እንቅስቃሴ በ40 ሺህ 381 ሄክታር መሬት ዝርያቸው የተሻሻሉ ፍራፍሬዎች በኩታ ገጠም እየለሙ መሆኑን ገልጸው በልማቱም ከ62 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ከግብርና ማዕከላት የወጡ ዝርያቸው የተሻሻሉና በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዛትና ጥራት ያለው ምርት የሚሰጡ ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያና ሌሎች ፍራፍሬዎች ለአርሶ አደሮቹ ተደራሽ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ እየተከናወነ ከሚገኘው የፍራፍሬ ልማት ከሁለት ሚሊዮን 291 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት በየዓመቱ እየተሰበሰበ እንደሚገኝም አስረድተዋል፡፡ አርሶ አደሩ በአንድ ዙር ምርት በአማካኝ ከ30 ሺህ እስከ 50 ሺህ ብር ገቢ እያገኘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለአብነትም በተያዘው የምርት ዘመን ፍሬ መስጠት ከጀመረ ‘ሓሽ’ ከተባለ የአቮካዶ ዝርያ 76 ኩንታል ምርት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
የማዳበሪያ ፋብሪካው መገንባት ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያስችላል
Oct 29, 2025 43
ጎንደር፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በቅርቡ ይፋ ያደረገችው የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥና የዘርፉን የውጪ ምንዛሬ የማመንጨት አቅምን ማጎልበት እንደሚያስችል ተመላከተ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተመረቀበት ወቅት ጉባ ላይ ይፋ ካደረጓቸው ግዙፍ የግንባታ ፕሮጀክቶች መካከል የማዳበሪያ ፋብሪካው ተጠቃሽ ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲንና ምሁር ካህሌ ጀንበር (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ መንግስት ሜጋ ፕሮጀክቶችን በመተግበር የወሰደው ኢንሼቲቭ የኢትዮጵያን እድገት ለማፋጠን የሚያስችል ነው። በተለይ የማዳበሪያ ፋብሪካው መገንባት የድህነት ታሪክን በመሰረዝ አዲስ የታሪክ ምዕራፍን ለማብሰር ፋይዳው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል። የፋብሪካው ግንባታ ሲጠናቀቅም ማዳበሪያን በብዛትና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለማዳበሪያ ግዢ በየዓመቱ የምታወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ በማስቀረት ለሌሎች የልማት ስራዎች ለማዋል እንደሚያግዝም ተናግረዋል። በተጨማሪም ሀገሪቱ ወደ ውጪ የምትልከውን የግብርና ምርት በማሳደግ የዘርፉን የውጪ ምንዛሬ የማመንጨት አቅምን በማጎልበት በኩል ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ከፍ ያለ መሆኑን አስረድተዋል። በምግብ ራስን መቻል የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የህልውና ጉዳይ ነው ብለዋል። ምሁራን አርሶ አደሩ በሳይንሳዊ የማዳበሪያ አጠቃቀም ላይ ያለውን የእውቀትና የክህሎት ክፍተት በጥናትና ምርምር በመታገዝ የመለወጥ ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ጠቁመዋል። የጎንደር ዩኒቨርሲቲም የምርምር ምክረ ሃሳቦችን በማፍለቅና የኤክስቴንሽን ስርጸትን በማጎልበት አርሶ አደሩ ሳይንሳዊ የማዳበሪያ አጠቃቀምን በማሻሻል የሚጠበቀውን ምርት እንዲያመርት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታንና የመጀመሪያውን የጋዝ ማውጣት ስራ በማጠናቀቅ የማዳበሪያ ፋብሪካና የነዳጅ ማጣሪያ ለመገንባት የወሰደችው ቁርጠኛ አቋም የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት እንደሚያደርጋትም ምሁሩ አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ የሚገባትን የባሕር በር መጠየቋ ቅንጦት አይደለም - ምሁራን
Oct 29, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ መልማቷን ባልፈለጉ አካላትና ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በትላንትናው እለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀይ ባሕር ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባሕር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ-ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ኢትዮጵያ ታምናለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ የወሰነው ማን ነው ብለን ስንፈትሽ ማስረጃ አልተገኘም፤ ተቋማትም እንዳልገቡበት አንስተዋል። ባሕር በር የኅልውና ጉዳይ በመሆኑ ኢትዮጵያም ተዘግቶባት መኖር ስለማትችል ጥረቷ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን በጉዳዩ ላይ እንዳሉት ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን ባልፈለጉ አካላት በተንኮል የተነጠቀችውን የአካሏን ክፋይ መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ አስረድተዋል። የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን ያጣችበት ሂደት ግፍ እንጂ ሕጋዊ አለመሆኑን አንስተው፤ መንግሥት ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት አምኖ አጀንዳ ማድረጉ ከሕግም ሆነ ከሞራል አንጻር ትክክል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንድታጠናክርም መክረዋል። በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ ያሬድ አያሌው (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚ መሆን ፋይዳው የቀጣናውም ጭምር እንደሚሆን አስረድተዋል። ቀጣናውን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያ የጠየቀችው የአካሏን ክፋይና ህጋዊ መብት መሆኑን በመገንዘብ ለጋራ ተጠቃሚነት ሲሉ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Oct 29, 2025 35
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር በመሰረተ ልማት ያላትን ትስስር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላትም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስቴር ፒዬንግ ዴንግ ኩኦል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ልዑካን ቡድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን በተለይም በአቢዬ ግዛት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ገለጻ አድርጓል። ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አጠናቃ በስኬት በማስመረቋ ደስታቸውን በመግለጽ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት በህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ በመሳተፋቸውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በመሰረተ ልማት የበለጠ በመተሳሰር ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጎልበት ሊሰሩ እንደሚገባም መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ የሚገባትን የባሕር በር መጠየቋ ቅንጦት አይደለም - ምሁራን
Oct 29, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ መልማቷን ባልፈለጉ አካላትና ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በትላንትናው እለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀይ ባሕር ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባሕር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ-ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ኢትዮጵያ ታምናለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ የወሰነው ማን ነው ብለን ስንፈትሽ ማስረጃ አልተገኘም፤ ተቋማትም እንዳልገቡበት አንስተዋል። ባሕር በር የኅልውና ጉዳይ በመሆኑ ኢትዮጵያም ተዘግቶባት መኖር ስለማትችል ጥረቷ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን በጉዳዩ ላይ እንዳሉት ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን ባልፈለጉ አካላት በተንኮል የተነጠቀችውን የአካሏን ክፋይ መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ አስረድተዋል። የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን ያጣችበት ሂደት ግፍ እንጂ ሕጋዊ አለመሆኑን አንስተው፤ መንግሥት ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት አምኖ አጀንዳ ማድረጉ ከሕግም ሆነ ከሞራል አንጻር ትክክል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንድታጠናክርም መክረዋል። በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ ያሬድ አያሌው (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚ መሆን ፋይዳው የቀጣናውም ጭምር እንደሚሆን አስረድተዋል። ቀጣናውን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያ የጠየቀችው የአካሏን ክፋይና ህጋዊ መብት መሆኑን በመገንዘብ ለጋራ ተጠቃሚነት ሲሉ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና በፍትህ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Oct 28, 2025 153
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቻይና በፍትህ ዘርፍ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የቻይና-አፍሪካ የዐቃብያነ ሕግ የትብብር ፎረም በቻይና ጓንዶንግ ግዛት ጓንጁ ከተማ ጥቅምት 19 እና 20 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። በፍትሕ ሚኒስትር ሀና አርዓያሥላሴ የሚመራ ልዑክ በስብስባው ላይ ይሳተፋል። የፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ዳባ በልዑካን ቡድኑ ተካተዋል። የፍትህ ሚኒስትር ሀና አርዓያሥላሴ ከቻይና ሉዓላዊ ሕዝብ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዪንግ ዮንግ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም ላይ ኢትዮጵያና ቻይና የቀደምት ሥልጣኔ ተምሳሌት እና 55 አመታት ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸው ተነስቷል። በሁለቱ ሀገራት መካከል የፍርደኞች ማዘዋወር እና በወንጀል ጉዳዮች የጋራ ትብብር የተደረጉ ስምምነቶችን ለመተግበር በሁለቱም ወገን እንደሚሰራ ተገልጿል። በኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር እና በቻይና ፍትህ ሚኒስቴር መካከል የአቅም ግንባታ ስራዎችን ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት የተፈረመ መሆኑን በማስታወስ በቀጣይ በበለጠ ትብብር ለመስራት ተስማምተዋል። የቻይናው ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዪንግ ዮንግ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ መሆኗን አንስተው፤ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ወዳጅነት በመጠቀም ቻይና ከአፍሪካ ጋር ላላት ግንኙነት እንደ መግቢያ በር እንደምትታይ አመልክተዋል። በቀጣይ የቻይና መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር የሚኖረውን ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክር መግለጻቸውን የፍትህ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
በየተቋማችን የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ እንተጋለን - የመንግስት ሠራተኞች
Oct 28, 2025 114
ጎንደር/ ገንዳ ውሃ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡- በሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፏቸውን በማጎልበት በየተቋማቸው የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በትጋት እንደሚሰሩ በጎንደር ከተማ የመንግስት ሠራተኞች ገለጹ። ሠራተኞቹ "የውጭ ባንዳዎችንና የውስጥ ባንዳዎችን ቅዠት በማምከን አንፀባራቂ ድሎችን እናስመዘግባለን " በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ሠራተኞቹ እንዳሉት፤ አገልግሎት አሠጣጥን በማዘመን ቀልጣፋና ፈጣን ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ይሰራሉ። ከተሳታፊዎቹ መካከል አስካል ፀሐይ በሰጡት አስተያየት፤ የመንግስት ተቋማትን የአገልግሎት አሠጣጥ ለማዘመን የተጀመሩ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮች የተገልጋዩን እንግልትና ቅሬታ የሚፈታ መሆኑን አንስተዋል። ይህም የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ከመሰረቱ የሚፈታና ሠራተኛውም በተመደበበት መስክ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ምቹ የስራ ምህዳር የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ ሌላኛው ተሳታፊ መልካሙ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሠራተኛውን የስራ ተነሳሽነት የሚያጎለብትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እውቀቱንም ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት በተመረጡ ተቋማት የጀመራቸው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ ወደ ሁሉም ተቋማት እንዲሠፉ የሚደግፉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዲጂታል ቴክኖሎጂው የተገልጋዩን ጊዜ ፣ገንዘብንና ጉልበትን ቆጥቦ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ያሉት ደግሞ አቶ ባዘዘው ታምራት ናቸው፡፡ ሠራተኞቹ በሰላም ግንባታ ላይ ሲያደርጉ የቆዩትን ተሳትፎ በማጎልበት በየተቋማቸው የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በታማኝነትና በቅንነት ተግተው እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሲርቪስና የሰው ሃብት ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ነጻነት መንግስቴ እንደገለጹት፤ መሶብ የአንድ ማዕከልን ጨምሮ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋና ፈጣን ማድረግ የሚያስችል ነው፡፡ በመንግስት ለሠራተኛው የተደረገው የደመወዝ ማሻሻያ የስራ ተነሳሽነቱን የሚያጎለብት በመሆኑ ሠራተኛው በሠላም ግንባታና በልማት እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክር አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይ የምዕራብ ጎንደር ዞን የመንግስት ሠራተኞች ውይይት አካሄደዋል። በገንዳውሃ በተካሄደው ውይይት ከተሳተፉት ሠራተኞች መካከል ዮሐንስ ዓለሙ የውጭና የውስጥ ጠላቶችን ሴራ በአንድነት በማክሸፍ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ሌላው ተሳታፊ ግርማ ሰፊው ፤ ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባሻገር አፍራሽ አጀንዳዎችን ቀድሞ በመገንዘብ ለመመከት ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ አቋም በመያዝ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ የተናገሩት ደግሞ አትጠገብ አሻግሬ ናቸው። የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ቢተው አሳየ በበኩላቸው፤ ነጠላ ትርክትን በማስወገድ ሀገሪቱ የያዘችውን የእድገት ጎዳና ማስቀጠልና ሰላምን ማፅናት ከሁሉም የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን አብራርተዋል። የመንግሥት ሠራተኛው ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት በመስጠት የሕብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ መትጋት እንዳለበት አሳስበዋል።
በሐረሪ ክልል የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 28, 2025 121
ሐረር ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በትኩረት ሊከናወኑ በሚገባቸው ተግባራት ዙሪያ ለክልሉ አመራር አባላት አቅጣጫ ሰጥተዋል። በወቅቱም ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። ህገወጥ የመሬት ወረራና የቤት ግንባታ እንዲሁም ህገ ወጥ ንግድን የመከላከሉና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ተግባር በአመራሩ በትኩረት ሊከናወኑ ከሚገባቸው ተግባራት መካከል እንደሆኑም ጠቅሰዋል። በክልሉ በአሁኑ ወቅት የተጀመሩና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት የማብቃት ስራ ላይ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። እንዲሁም በኮሪደር ልማት የተጀመሩ ስራዎች በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ የማጠናቀቅ ስራን ማከናወን ይገባል ሲሉም አክለዋል። በበጀት ዓመቱ አዲስ በዕቅድ የተያዙ የወንዝ ዳርቻ ልማትና ሌሎች ስራዎችን በፍጥነት ወደ ስራ የማስገባት ተግባር ይከናወናል ብለዋል። ከዚህም በተጨማሪ የገጠሩን ማህበረሰብ ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ በምርት አሰባሰብ ወቅት የምርት ብክነት እንዳይከሰት በማድረግ አርሶ አደሩ ምርቱን ለገበያ እስኪያቀርብ ድረስ ክትትል እና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉም አክለዋል። በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ የመሰብሰብ ስራን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ተናግረዋል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ለማህበረሰቡ የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ስራን ማሳለጥ እንደሚገባም አመልክተዋል።
የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው
Oct 28, 2025 167
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፣ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊ (ጂኦግራፊያዊ)፣ ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት 30 ዓመት በላይ የወሰደ ትግል እንደነበር ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አገሪቷ ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ 30 ዓመት አያስፈልጋትም ብለዋል። ይህን ጉዳይ ለመፍታት በተረጋጋ፣ በሰከነ እና በውይይት መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ "ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅብንም" ሲሉ በአጽንኦት ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልወሰነው፣ ተወካዮች ያላዩትና ካቢኔም ያልወሰነው ውሳኔ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ትልቅ ጉዳይ ማን ወሰነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ህጋዊ እና ተቋማዊ መሠረት የሌለው ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን በተከተለ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችውን ጥረት እንደግፋለን-የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Oct 28, 2025 165
ወላይታ ሶዶ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን ተከትላ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ በቁርጠኝነት እንደሚደግፉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀመው የቆየው የባህር በር በታሪክ አጋጣሚ ከእጇ ወጥቶ ከወደብ አልባ ሀገራት ተርታ ተሰልፋ ቆይታለች። መንግስትም የኢትዮጵያዊያን የዘመናት ቁጭት ሆኖ የቆየውን የባህር በር ጥያቄ በይፋ በማንሳት በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል። ይህንንም የኢፌድሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮችና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር አጽንኦት መስጠታቸው የሚታወስ ነው። በጉዳዩ ላይ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት የባህር በር ጥያቄው የትውልዱ የዘመናት ቁጭትን የሚመልስ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ መንግስት የጀመረው ጥረት እንዲሳካ በቁርጠኝነት እንደሚደግፉ ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ጎበዜ አበራ የባህር በር ለሀገር ሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት መሰረት መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን በተከተለና ዲፕሎማሲየዊ በሆነ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት እንዲሳካም ምክር ቤቱ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። "ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀምበት የነበረውን የባህር በር ማጣቷ ለድህነታችን አንድ ምክንያት ከመሆኑ በላይ የሚያስቆጭ ነው" ያሉት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ አቶ ተፈራ ጎበና ናቸው። የባህር በር ጥያቄን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶችን ማጠናከር ለድርድር መቅረብ የለበትም ያሉት አቶ ተፈራ የጉዳዩ መሳካት ልማትና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማፋጠን አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። የባህር በር ለማግኘት መንግስት የጀመረው ተግባር ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ እውን እንዲሆን ፓርቲያቸው የሚጠበቅበትን ይወጣል ሲሉም ገልጸዋል። የወላይታ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ወህዴግ) ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሚልክያስ ሳንታ በበኩላቸው መንግስት የባህር በር ለማግኘት የጀመረው ተግባር ወቅቱን የጠበቀ ትክክለኛ አካሄድ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በታሪክም ይሁን በህግ ተገቢነት እንዳለው አንስተው ጉዳዩም የትውልዱ ጭምር መሆኑን አንስተዋል። መንግስት ለኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚያስፈልግ በይፋ መናገር ከጀመረ ወዲህ በዓለም አቀፍ ደረጃም አጀንዳ እየሆነ መምጣቱ ጥሩ ስኬት መሆኑን ጠቅሰው፣ ለስኬታማነቱም በተለይ የኢትዮጵያ አጎራባች ሀገራት ተባባሪ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል። የባህር በር መኖር ሀገሪቱ አሁን እያስመዘገበች ያለውን ፈጣን ዕድገት አጠናክሮ የማስቀጠል ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አቶ ሚልክያስ አንስተዋል። በመሆኑም ጥያቄው ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ በግልም ሆነ እንደ ፓርቲ ያላሰለሰ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ የቀረበለትን የድጋፍ ሞሽን አፀደቀ
Oct 28, 2025 146
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የቀረበውን የ2018 የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫ የድጋፍ ሞሽን አፅድቋል። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ አካሂዷል። በፕሬዝዳንቱ የቀረበውን ሞሽን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። ምክር ቤቱም የቀረበለትን የድጋፍ ሞሽን አፅድቋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Oct 29, 2025 35
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር በመሰረተ ልማት ያላትን ትስስር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላትም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስቴር ፒዬንግ ዴንግ ኩኦል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ልዑካን ቡድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን በተለይም በአቢዬ ግዛት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ገለጻ አድርጓል። ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አጠናቃ በስኬት በማስመረቋ ደስታቸውን በመግለጽ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት በህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ በመሳተፋቸውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በመሰረተ ልማት የበለጠ በመተሳሰር ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጎልበት ሊሰሩ እንደሚገባም መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ የሚገባትን የባሕር በር መጠየቋ ቅንጦት አይደለም - ምሁራን
Oct 29, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ መልማቷን ባልፈለጉ አካላትና ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በትላንትናው እለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀይ ባሕር ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባሕር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ-ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ኢትዮጵያ ታምናለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ የወሰነው ማን ነው ብለን ስንፈትሽ ማስረጃ አልተገኘም፤ ተቋማትም እንዳልገቡበት አንስተዋል። ባሕር በር የኅልውና ጉዳይ በመሆኑ ኢትዮጵያም ተዘግቶባት መኖር ስለማትችል ጥረቷ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን በጉዳዩ ላይ እንዳሉት ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን ባልፈለጉ አካላት በተንኮል የተነጠቀችውን የአካሏን ክፋይ መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ አስረድተዋል። የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን ያጣችበት ሂደት ግፍ እንጂ ሕጋዊ አለመሆኑን አንስተው፤ መንግሥት ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት አምኖ አጀንዳ ማድረጉ ከሕግም ሆነ ከሞራል አንጻር ትክክል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንድታጠናክርም መክረዋል። በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ ያሬድ አያሌው (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚ መሆን ፋይዳው የቀጣናውም ጭምር እንደሚሆን አስረድተዋል። ቀጣናውን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያ የጠየቀችው የአካሏን ክፋይና ህጋዊ መብት መሆኑን በመገንዘብ ለጋራ ተጠቃሚነት ሲሉ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና በፍትህ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Oct 28, 2025 153
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቻይና በፍትህ ዘርፍ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የቻይና-አፍሪካ የዐቃብያነ ሕግ የትብብር ፎረም በቻይና ጓንዶንግ ግዛት ጓንጁ ከተማ ጥቅምት 19 እና 20 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። በፍትሕ ሚኒስትር ሀና አርዓያሥላሴ የሚመራ ልዑክ በስብስባው ላይ ይሳተፋል። የፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ዳባ በልዑካን ቡድኑ ተካተዋል። የፍትህ ሚኒስትር ሀና አርዓያሥላሴ ከቻይና ሉዓላዊ ሕዝብ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዪንግ ዮንግ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም ላይ ኢትዮጵያና ቻይና የቀደምት ሥልጣኔ ተምሳሌት እና 55 አመታት ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸው ተነስቷል። በሁለቱ ሀገራት መካከል የፍርደኞች ማዘዋወር እና በወንጀል ጉዳዮች የጋራ ትብብር የተደረጉ ስምምነቶችን ለመተግበር በሁለቱም ወገን እንደሚሰራ ተገልጿል። በኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር እና በቻይና ፍትህ ሚኒስቴር መካከል የአቅም ግንባታ ስራዎችን ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት የተፈረመ መሆኑን በማስታወስ በቀጣይ በበለጠ ትብብር ለመስራት ተስማምተዋል። የቻይናው ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዪንግ ዮንግ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ መሆኗን አንስተው፤ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ወዳጅነት በመጠቀም ቻይና ከአፍሪካ ጋር ላላት ግንኙነት እንደ መግቢያ በር እንደምትታይ አመልክተዋል። በቀጣይ የቻይና መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር የሚኖረውን ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክር መግለጻቸውን የፍትህ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
በየተቋማችን የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ እንተጋለን - የመንግስት ሠራተኞች
Oct 28, 2025 114
ጎንደር/ ገንዳ ውሃ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡- በሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፏቸውን በማጎልበት በየተቋማቸው የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በትጋት እንደሚሰሩ በጎንደር ከተማ የመንግስት ሠራተኞች ገለጹ። ሠራተኞቹ "የውጭ ባንዳዎችንና የውስጥ ባንዳዎችን ቅዠት በማምከን አንፀባራቂ ድሎችን እናስመዘግባለን " በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ሠራተኞቹ እንዳሉት፤ አገልግሎት አሠጣጥን በማዘመን ቀልጣፋና ፈጣን ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ይሰራሉ። ከተሳታፊዎቹ መካከል አስካል ፀሐይ በሰጡት አስተያየት፤ የመንግስት ተቋማትን የአገልግሎት አሠጣጥ ለማዘመን የተጀመሩ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮች የተገልጋዩን እንግልትና ቅሬታ የሚፈታ መሆኑን አንስተዋል። ይህም የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ከመሰረቱ የሚፈታና ሠራተኛውም በተመደበበት መስክ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ምቹ የስራ ምህዳር የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ ሌላኛው ተሳታፊ መልካሙ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሠራተኛውን የስራ ተነሳሽነት የሚያጎለብትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እውቀቱንም ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት በተመረጡ ተቋማት የጀመራቸው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ ወደ ሁሉም ተቋማት እንዲሠፉ የሚደግፉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዲጂታል ቴክኖሎጂው የተገልጋዩን ጊዜ ፣ገንዘብንና ጉልበትን ቆጥቦ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ያሉት ደግሞ አቶ ባዘዘው ታምራት ናቸው፡፡ ሠራተኞቹ በሰላም ግንባታ ላይ ሲያደርጉ የቆዩትን ተሳትፎ በማጎልበት በየተቋማቸው የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በታማኝነትና በቅንነት ተግተው እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሲርቪስና የሰው ሃብት ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ነጻነት መንግስቴ እንደገለጹት፤ መሶብ የአንድ ማዕከልን ጨምሮ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋና ፈጣን ማድረግ የሚያስችል ነው፡፡ በመንግስት ለሠራተኛው የተደረገው የደመወዝ ማሻሻያ የስራ ተነሳሽነቱን የሚያጎለብት በመሆኑ ሠራተኛው በሠላም ግንባታና በልማት እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክር አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይ የምዕራብ ጎንደር ዞን የመንግስት ሠራተኞች ውይይት አካሄደዋል። በገንዳውሃ በተካሄደው ውይይት ከተሳተፉት ሠራተኞች መካከል ዮሐንስ ዓለሙ የውጭና የውስጥ ጠላቶችን ሴራ በአንድነት በማክሸፍ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ሌላው ተሳታፊ ግርማ ሰፊው ፤ ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባሻገር አፍራሽ አጀንዳዎችን ቀድሞ በመገንዘብ ለመመከት ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ አቋም በመያዝ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ የተናገሩት ደግሞ አትጠገብ አሻግሬ ናቸው። የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ቢተው አሳየ በበኩላቸው፤ ነጠላ ትርክትን በማስወገድ ሀገሪቱ የያዘችውን የእድገት ጎዳና ማስቀጠልና ሰላምን ማፅናት ከሁሉም የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን አብራርተዋል። የመንግሥት ሠራተኛው ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት በመስጠት የሕብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ መትጋት እንዳለበት አሳስበዋል።
በሐረሪ ክልል የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 28, 2025 121
ሐረር ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በትኩረት ሊከናወኑ በሚገባቸው ተግባራት ዙሪያ ለክልሉ አመራር አባላት አቅጣጫ ሰጥተዋል። በወቅቱም ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። ህገወጥ የመሬት ወረራና የቤት ግንባታ እንዲሁም ህገ ወጥ ንግድን የመከላከሉና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ተግባር በአመራሩ በትኩረት ሊከናወኑ ከሚገባቸው ተግባራት መካከል እንደሆኑም ጠቅሰዋል። በክልሉ በአሁኑ ወቅት የተጀመሩና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት የማብቃት ስራ ላይ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። እንዲሁም በኮሪደር ልማት የተጀመሩ ስራዎች በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ የማጠናቀቅ ስራን ማከናወን ይገባል ሲሉም አክለዋል። በበጀት ዓመቱ አዲስ በዕቅድ የተያዙ የወንዝ ዳርቻ ልማትና ሌሎች ስራዎችን በፍጥነት ወደ ስራ የማስገባት ተግባር ይከናወናል ብለዋል። ከዚህም በተጨማሪ የገጠሩን ማህበረሰብ ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ በምርት አሰባሰብ ወቅት የምርት ብክነት እንዳይከሰት በማድረግ አርሶ አደሩ ምርቱን ለገበያ እስኪያቀርብ ድረስ ክትትል እና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉም አክለዋል። በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ የመሰብሰብ ስራን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ተናግረዋል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ለማህበረሰቡ የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ስራን ማሳለጥ እንደሚገባም አመልክተዋል።
የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው
Oct 28, 2025 167
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፣ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊ (ጂኦግራፊያዊ)፣ ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት 30 ዓመት በላይ የወሰደ ትግል እንደነበር ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አገሪቷ ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ 30 ዓመት አያስፈልጋትም ብለዋል። ይህን ጉዳይ ለመፍታት በተረጋጋ፣ በሰከነ እና በውይይት መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ "ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅብንም" ሲሉ በአጽንኦት ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልወሰነው፣ ተወካዮች ያላዩትና ካቢኔም ያልወሰነው ውሳኔ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ትልቅ ጉዳይ ማን ወሰነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ህጋዊ እና ተቋማዊ መሠረት የሌለው ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን በተከተለ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችውን ጥረት እንደግፋለን-የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Oct 28, 2025 165
ወላይታ ሶዶ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን ተከትላ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ በቁርጠኝነት እንደሚደግፉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀመው የቆየው የባህር በር በታሪክ አጋጣሚ ከእጇ ወጥቶ ከወደብ አልባ ሀገራት ተርታ ተሰልፋ ቆይታለች። መንግስትም የኢትዮጵያዊያን የዘመናት ቁጭት ሆኖ የቆየውን የባህር በር ጥያቄ በይፋ በማንሳት በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል። ይህንንም የኢፌድሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮችና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር አጽንኦት መስጠታቸው የሚታወስ ነው። በጉዳዩ ላይ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት የባህር በር ጥያቄው የትውልዱ የዘመናት ቁጭትን የሚመልስ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ መንግስት የጀመረው ጥረት እንዲሳካ በቁርጠኝነት እንደሚደግፉ ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ጎበዜ አበራ የባህር በር ለሀገር ሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት መሰረት መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን በተከተለና ዲፕሎማሲየዊ በሆነ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት እንዲሳካም ምክር ቤቱ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። "ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀምበት የነበረውን የባህር በር ማጣቷ ለድህነታችን አንድ ምክንያት ከመሆኑ በላይ የሚያስቆጭ ነው" ያሉት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ አቶ ተፈራ ጎበና ናቸው። የባህር በር ጥያቄን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶችን ማጠናከር ለድርድር መቅረብ የለበትም ያሉት አቶ ተፈራ የጉዳዩ መሳካት ልማትና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማፋጠን አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። የባህር በር ለማግኘት መንግስት የጀመረው ተግባር ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ እውን እንዲሆን ፓርቲያቸው የሚጠበቅበትን ይወጣል ሲሉም ገልጸዋል። የወላይታ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ወህዴግ) ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሚልክያስ ሳንታ በበኩላቸው መንግስት የባህር በር ለማግኘት የጀመረው ተግባር ወቅቱን የጠበቀ ትክክለኛ አካሄድ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በታሪክም ይሁን በህግ ተገቢነት እንዳለው አንስተው ጉዳዩም የትውልዱ ጭምር መሆኑን አንስተዋል። መንግስት ለኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚያስፈልግ በይፋ መናገር ከጀመረ ወዲህ በዓለም አቀፍ ደረጃም አጀንዳ እየሆነ መምጣቱ ጥሩ ስኬት መሆኑን ጠቅሰው፣ ለስኬታማነቱም በተለይ የኢትዮጵያ አጎራባች ሀገራት ተባባሪ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል። የባህር በር መኖር ሀገሪቱ አሁን እያስመዘገበች ያለውን ፈጣን ዕድገት አጠናክሮ የማስቀጠል ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አቶ ሚልክያስ አንስተዋል። በመሆኑም ጥያቄው ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ በግልም ሆነ እንደ ፓርቲ ያላሰለሰ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ የቀረበለትን የድጋፍ ሞሽን አፀደቀ
Oct 28, 2025 146
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የቀረበውን የ2018 የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫ የድጋፍ ሞሽን አፅድቋል። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ አካሂዷል። በፕሬዝዳንቱ የቀረበውን ሞሽን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። ምክር ቤቱም የቀረበለትን የድጋፍ ሞሽን አፅድቋል።
ማህበራዊ
አዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን ዝግጅት እያደረገ ነው
Oct 29, 2025 41
አዳማ ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- አዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን የቅድመ ዝግጅት ተግባር እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ለሚ ጉታ(ዶ/ር) ፤ ተቋሙ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ለሀገር እድገት በሚገባው ልክ አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ራስ ገዝ ለመሆን እየተዘጋጀ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ተከትሎ ራስ ገዝ ለመሆን የትምህርት ሚኒስቴር መስፈርቶችን ማሟላት በሚያስችል አግባብ ላይ እንደሆነ ተናግረዋል። ከዝግጅቱም ውስጥ የተቋማዊ ግምገማ ሠነድ፣ ስትራቴጂክ እቅድ፣ፖሊሲና መመሪያዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። ይህንንም ተከትሎ ዩኒቨርስቲው ራስ ገዝ (የአውቶኖመስ) የመሆን ጥያቄውን ለትምህርት ሚኒስቴር በይፋ ማቅረቡን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስታውቀዋል። በተለይ የመማር ማስተማር፣የምርምር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይም ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከነዚህ ስራዎች ውስጥ ባለፈው በጀት ዓመት የተጠናቀቀው የምርምር ፓርክ ግንባታን አንስተዋል። በዚህ የምርምር ፓርክ ውስጥ ለሚገኙ አምስት የልህቀት ማዕከላት 30 ቤተ ሙከራዎችን የማደራጀት ስራ ተጀምሯል ብለዋል። ይህ ፓርክ ከዩኒቨርሲቲው ባሻገር እንደ ሀገር በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ግዙፍ እና ልዩ የምርምር ማዕከል በመሆን የላቀ ፋይዳ እንደሚኖረው አስረድተዋል። በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው ዘመናዊ የዳታ ማዕከል፣የ10 ኪሎ ሜትር አስፋልት እና አራት ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መንገድና ሌሎችም ግንባታዎች እየተገባደዱ ይገኛሉ ብለዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1294/2015 በአብላጫ ደምፅ ማጽደቁ ይታወሳል። አዋጁ ለሀገር ዕድገት ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በምርምር የላቀ እውቀት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት የሚሰሩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ለመገንባት ያለመ ነው። ከዚህም ባለፈ ዩኒቨርሲቲዎቹ ሙያዊ ተልዕኳቸውን በላቀ ብቃት ተመራማሪዎችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ። የጥናትና ምርምር፣ የትምህርትና የማህበረሰባዊ ነጻ አገልግሎት የሚያከናውኑበትን የፋይናንስ ምንጭ መሰብሰብና ሀገራዊ ልማትን ማገዝ የሚችሉበትን ነጻ ምህዳር ለመፍጠር ትልቅ ዕገዛ እንዲኖረው ተደርጎ በውይይት ዳብሮ መዘጋጀቱን በወቅቱ ተጠቅሷል።
በመዲናዋ የተማሪዎችን ውጤት ለማላቅ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ትውልድን ለማነፅ አቅም ፈጥረዋል
Oct 29, 2025 44
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦በመዲናዋ የተማሪዎችን ውጤት ለማላቅ የተከናወኑ ተግባራት የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ውጤታማ ትውልድን ለማነፅ አቅም መፍጠራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ትናንት ለምክር ቤቱ አባላት በሀገሪቱ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በትምህርት ለትውልድ እንቅስቃሴ የትምህርት ተቋማትን ምቹ የማድረግና የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች ተደራሽ በማድረግ እንዲሁም የተማሪዎች የምገባ መርሀ ግብር ማከናወኑ እየሰራቸው ካሉ ተግባራቶች ውስጥ ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተዋል። በዘንድሮው የትምህርት ዘመንም ከ43 ሚሊየን በላይ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የመማሪያ መጻሕፍት መታደሉንና ይህም የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ከተሰሩ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆኑን ገልፀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በመዲናዋ ትውልድን የሚያንጹ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን አስታውቀዋል። ከተማ አስተዳደሩ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ትምህርት ቤቶችን በመሰረተ ልማት ምቹ የማድረግ፣ የግብዓት አቅርቦትና የተማሪዎች ምገባን የማጠናከር ስራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በትምህርት ለትውልድ እንቅስቃሴ ከተለያዩ አካላት ሀብት በማሰባሰብ የትምህርት ተቋማትን መሰረታዊ ችግሮች መፍታት መቻሉን ተናግረዋል። የምገባና የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን በወቅቱ ማቅረብ በመቻሉ ተማሪዎች ትምህርታቸው ላይ ትኩረት እንዲያደርጉና የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ማስቻሉንም ገልጸዋል። ትምህርት ቢሮው በከተማዋ ያሉ የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስቀድመው ሰፋ ያለ ዝግጅት እንዲኖራቸው ለማድረግ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ማላቂያ ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ገብቷል ብለዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምገባ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ስንታየሁ ማሞ በበኩላቸው በተያዘው ዓመት ተማሪዎች በወቅቱ የትምህርት ግብአት እንዲያገኙና የምገባ መርሀ ግብር በጊዜው እንዲጀመር መደረጉን ገልፀዋል። በዚህም በ253 ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ከ976 ሺህ በላይ ተማሪዎች የምገባ መርሀ ግብሩ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከ1 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የዩኒፎርምና የደብተር አቅርቦት ተደራሽ መደረጉንም አብራርተዋል። የለም አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርእሰ መምህር ሰለሞን ዲሮ በትምህርት ለትውልድ እንቅስቃሴ ትምህርት ቤቱ ከግብአትና ከመሰረተ ልማት አኳያ የነበሩበትን ችግሮች የትምህርት ቤቱን ማህበረሰብ፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና አጋር አካላትን በማሳተፍ መቅረፍ መቻሉን ተናግረዋል። ከተሰሩ ስራዎች መካከልም የላብራቶሪ እቃዎች፣የቤተ መጽሀፍትን ሌሎች ለመማር ማስተማር ሂደት አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ማሟላት ተጠቃሽ መሆኑን በመግለጽ ይህም ተማሪዎች በትምህርታቸው ላይ የተሻለ እውቀት እንዲገበዩ አቅም ፈጥሯል ብለዋል። ትምህርት ቤቱ በዘንድሮ የትምህርት ዘመን 426 የቅድመ መጀመሪያ ደረጃ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ ይገኛል ያሉት ደግሞ የአዲስ ራዕይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርት እየሩሳሌም ተሾመ ናቸው። መንግሥት ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች በሰጠው ልዩ ትኩረት ህጻናት በተሟላ ግብዓት እና በአማረ ሁኔታ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ መደረጉን ገልፀዋል። በተለይም የተማሪዎች ምገባ መርሀ ግብር ህጻናት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ ማስቻሉን ተናግረዋል።
መንግስት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የወሰዳቸው እርምጃዎችና የተከተላቸው ስትራቴጂዎች ውጤት አምጥተዋል
Oct 28, 2025 209
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦መንግስት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የወሰዳቸው እርምጃዎችና የተከተላቸው ስትራቴጂዎች ውጤት አምጥተዋል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 ዓ.ም አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት ሰጥቷል፡፡ ሽልማቱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለተማሪዎቹ አስረክበዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፣ መንግስት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን አዲስ ፖሊሲ እና ሥርዓተ ትምህርት በመቅረጽ ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል ብለዋል፡፡ ይህም የመማር ማስተማር ሥርዓቱን ምቹ በማድረግ እና የትምህርት ግብዓቶችን በማቅረብ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡ መንግስት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የወሰዳቸው እርምጃዎችና የተከተላቸው ስትራቴጂዎች የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤት አምጥተዋል ብለዋል፡፡ የተማሪዎች ውጤት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እና እያደገ መምጣቱን ነው የተናገሩት፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው ውጤት ለዘርፉ ትኩረት ከተሰጠ የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን በአጭር ጊዜ ማሳካት እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በቀጣይ የመጣውን ውጤት እያበረታታን ለሌላ ስኬት ጠንክረን የምንሠራ ይሆናል ነው ያሉት። ተማሪዎች ዛሬ የተሰጣቸው ሽልማት በቀጣይ ሕይወታቸው ጠንክረው በመስራት ለአገራቸው የበኩላቸውን የላቀ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በ2017 ዓ.ም የተመዘገበው ውጤት መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት ትሩፋት ነው ብለዋል፡፡ ለተገኘው ውጤት የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ ሚና ማበርከቱን አንስተዋል፡፡ በ2018 ዓ.ም ከዚህ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ቢሮው ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ለተግባራዊነቱም ባለድርሻ አካላት ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡ ኢዜአ ካነጋገራቸው ተሸላሚ ተማሪዎች መካከል ናኢም ለገሰ፤ሽልማቱ ለቀጣይ ህይወቴ ስንቅ የሚሆንና ከኛ ቀጥለው ለሚመጡ ተማሪዎች ደግሞ ተስፋ የሚሆን ነው ብሏል፡፡ ሌላኛው ተሸላሚ ተማሪ ዳዊት ፈይሳ በበኩሉ፤ እውቅናው እኛ እንድንበረታ እና በቀጣይ ለሀገራችን የተሻለ ስራ እንድንሰራ የሚያነሳሳን ነው ብሏል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ የሰጠን እውቅና ሃላፊነት እንዲሰማንና ለበለጠ ስራ እንድንተጋ ያደርገናል ያለችው ደግሞ ሌላኛዋ ተሸላሚ ተማሪ እየሩሳሌም ያየሰው ናት፡፡ ለተመዘገበው የተማሪዎች የላቀ ውጤት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና የትምህርት ማኅበረሰብ አባላት እውቅና ተሰጥቷል።
በአርባምንጭ ከተማ የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግ የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል
Oct 28, 2025 89
አርባምንጭ፤ ጥቅምት18/2018(ኢዜአ)፡-በአርባምንጭ ከተማ የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግ የሚያስችል አሰራር በየደረጃው መዘርጋቱን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ። በከተማው አስተዳደር የመንግስት ተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያቀላጥፍ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የአንድ መስኮት አገልግሎት ዛሬ ተጀምሯል። አገልግሎቱን ያስጀመሩት የከተማው አስተዳደር ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) እና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች ናቸው። ከንቲባው፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን ለማቀላጠፍ በከተማው በሁሉም ቀበሌዎች የአንድ መስኮት አገልግሎት በሰው ሀይልና በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ መደራጀቱን ተናግረዋል። በከተማው በሁሉም ቀበሌዎች የተመቻቸው የአንድ መስኮት አገልግሎት የአስተዳደር ፣የንግድ ፣የገቢ ፣የማዘጋጃ ፣የፖሊስና ሌሎች ተቋማትን ያቀፈ በመሆኑ እንግልትንና የጊዜ ብክነትን በማስቀረት ሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል እንደሆነ ከንቲባው አብራርተዋል። ከአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ጩባ ጭኖ በሰጡት አስተያየት፤ አስተዳደሩ ከተማውን የሚመጥንና ሁሉንም ተደራሽ ያደረገ የተቋማት አገልግሎት ማመቻቸቱ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ይገጥማቸው ከነበረው እንግልትና የጊዜ ብክነት በመላቀቅ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል። የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን ከወረቀት ነፃ የሆነ አሰራር መመቻቸቱ መልካም መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ አልማዝ አንዳርጌ ናቸው።
ኢኮኖሚ
በምዕራብ ወለጋ ዞን የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን የተጠቀሙ አርሶ አደሮች ውጤታማ ሆነዋል
Oct 29, 2025 29
ጊምቢ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን ከግብርና ማዕከል የወጡ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን የተጠቀሙ አርሶ አደሮች ከልማቱ የተሻለ ገቢ በማግኘት ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በፍራፍሬ ልማት ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ከመንግስት ባገኙት የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን ተጠቅመው በማልማት ገቢ አግኝተው የተሻለ ኑሮ መምራት መጀመራቸውን ገልጸዋል። የተሻሻሉ ዝርያዎቹን ከተጠቀሙ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ የሆማ ወረዳ ነዋሪው አቶ ተካልኝ ኤፍሬም፣ ከዚህ በፊት በቡና ልማት ላይ ብቻ ጥገኛ ሆነው መቆየታቸውን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ ዝርያቸው የተሻሻሉ ፍራፍሬዎችን በመጠቀም በማልማታቸው ውጤታማ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። አቮካዶና ሙዝ በማልማት በዓመት እስከ 25 ሺህ ብር ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስተው በዚህም ህይወታቸውን በተሻለ መንገድ እየመሩ መሆኑን ተናግረዋል። የላሎ አሳቢ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር ገረመው ጅሬኛ በበኩላቸው ከግብርና ማዕከል የወጣ የተሻሻለ የሙዝ ዝርያን በማልማት ኢኮኖሚያቸው እያደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ ልማቱን በማጠናከር የሙዝ ዝርያዎችን በማባዛትና በማልማት ተጠቃሚነታቸውን የበለጠ ለማሳደግ ተግተው እንደሚሰሩም ጠቅሰዋል፡፡ በምዕራብ ወለጋ ዞን የግብርና ጽህፈት ቤት የፍራፍሬ ልማት ባለሙያ አቶ ጂብሪል መንጌ እንደገለጹት በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች የፍራፍሬ ልማት በሰፊው እየተካሄደ ነው። በእስካሁኑ እንቅስቃሴ በ40 ሺህ 381 ሄክታር መሬት ዝርያቸው የተሻሻሉ ፍራፍሬዎች በኩታ ገጠም እየለሙ መሆኑን ገልጸው በልማቱም ከ62 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ከግብርና ማዕከላት የወጡ ዝርያቸው የተሻሻሉና በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዛትና ጥራት ያለው ምርት የሚሰጡ ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያና ሌሎች ፍራፍሬዎች ለአርሶ አደሮቹ ተደራሽ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ እየተከናወነ ከሚገኘው የፍራፍሬ ልማት ከሁለት ሚሊዮን 291 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት በየዓመቱ እየተሰበሰበ እንደሚገኝም አስረድተዋል፡፡ አርሶ አደሩ በአንድ ዙር ምርት በአማካኝ ከ30 ሺህ እስከ 50 ሺህ ብር ገቢ እያገኘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለአብነትም በተያዘው የምርት ዘመን ፍሬ መስጠት ከጀመረ ‘ሓሽ’ ከተባለ የአቮካዶ ዝርያ 76 ኩንታል ምርት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
የማዳበሪያ ፋብሪካው መገንባት ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያስችላል
Oct 29, 2025 43
ጎንደር፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በቅርቡ ይፋ ያደረገችው የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥና የዘርፉን የውጪ ምንዛሬ የማመንጨት አቅምን ማጎልበት እንደሚያስችል ተመላከተ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተመረቀበት ወቅት ጉባ ላይ ይፋ ካደረጓቸው ግዙፍ የግንባታ ፕሮጀክቶች መካከል የማዳበሪያ ፋብሪካው ተጠቃሽ ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲንና ምሁር ካህሌ ጀንበር (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ መንግስት ሜጋ ፕሮጀክቶችን በመተግበር የወሰደው ኢንሼቲቭ የኢትዮጵያን እድገት ለማፋጠን የሚያስችል ነው። በተለይ የማዳበሪያ ፋብሪካው መገንባት የድህነት ታሪክን በመሰረዝ አዲስ የታሪክ ምዕራፍን ለማብሰር ፋይዳው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል። የፋብሪካው ግንባታ ሲጠናቀቅም ማዳበሪያን በብዛትና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለማዳበሪያ ግዢ በየዓመቱ የምታወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ በማስቀረት ለሌሎች የልማት ስራዎች ለማዋል እንደሚያግዝም ተናግረዋል። በተጨማሪም ሀገሪቱ ወደ ውጪ የምትልከውን የግብርና ምርት በማሳደግ የዘርፉን የውጪ ምንዛሬ የማመንጨት አቅምን በማጎልበት በኩል ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ከፍ ያለ መሆኑን አስረድተዋል። በምግብ ራስን መቻል የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የህልውና ጉዳይ ነው ብለዋል። ምሁራን አርሶ አደሩ በሳይንሳዊ የማዳበሪያ አጠቃቀም ላይ ያለውን የእውቀትና የክህሎት ክፍተት በጥናትና ምርምር በመታገዝ የመለወጥ ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ጠቁመዋል። የጎንደር ዩኒቨርሲቲም የምርምር ምክረ ሃሳቦችን በማፍለቅና የኤክስቴንሽን ስርጸትን በማጎልበት አርሶ አደሩ ሳይንሳዊ የማዳበሪያ አጠቃቀምን በማሻሻል የሚጠበቀውን ምርት እንዲያመርት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታንና የመጀመሪያውን የጋዝ ማውጣት ስራ በማጠናቀቅ የማዳበሪያ ፋብሪካና የነዳጅ ማጣሪያ ለመገንባት የወሰደችው ቁርጠኛ አቋም የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት እንደሚያደርጋትም ምሁሩ አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት የወሰደባትን 30 ዓመት ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ አያስፈልጋትም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 29, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት የወሰደባትን 30 ዓመታት ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ ሌላ 30 ዓመታት አያስፈልጋትም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ በተካሀደበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፣ ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት የወሰደባትን 30 ዓመታት ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ ሌላ 30 ዓመታት አያስፈልጋትም ብለዋል። የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ(ጂኦግራፊያዊ) እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት 30 ዓመት በላይ ያህል የወሰደ ትግል እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሀገሪቱ ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ 30 ዓመት አያስፈልጋትም ነው ያሉት። ይህን ጉዳይ ለመፍታት በተረጋጋ፣ በሰከነ እና በውይይት መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤ ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅብንም ሲሉም በአጽንኦት ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ካቢኔ ያልወሰነው፣ ተወካዮች ያላዩት መሆኑን ጠቁመው፤ ጥያቄው ይህን ትልቅ ጉዳይ ማን ወሰነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ህጋዊ እና ተቋማዊ መሠረት የሌለው እንደሆነም ነው የገለጹት።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሦስት ወራት ከ4 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ
Oct 29, 2025 43
ሆሳዕና፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በባለፉት ሦስት ወራት ከ4 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ገለፀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሻድ ለኢዜአ እንደገለጹት ቢሮው የክልሉን የገቢ አማራጮች በማስፋትና ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ የማህበረሰቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ አየሰራ ነው፡፡ የክልሉን 60 በመቶ ወጪ በውስጥ ገቢ ለመሸፈን ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ለዚህም በክልሉ ያለውን የገቢ አማራጭ ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከተለያዩ የገቢ አማራጮች 23 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን የጠቆሙት ወይዘሮ ቀመሪያ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ4 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል ብለዋል። የክልሉ የውስጥ ገቢ አቅም በየጊዜው እያደገ መምጣቱን የተናገሩት ሃላፊዋ ለዚህም የገቢ አሰባሰብ አሰራር መዘመን እና የማህበረሰቡ ግንዛቤ እያደገ መምጣቱን በምክንያትነት ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ ከአጠቃላይ ገቢ 47 በመቶ የሚሆነው ከተጨማሪ እሴት ታክስ ግብር ከፋዮች፣ ከቫትና ከደረሰኝ የሚሰበሰብ መሆኑን ገልጸው ህብረተሰቡ ስለግብር ያለው ግንዛቤ እያደገ ቢመጣም ደረሰኝ በመቀበል ረገድ ውስንነቶች አሉ ብልዋል።፡ ይህም ክልሉ ከሚያመነጨው ገቢ የሚጠበቅበትን መሰብሰብ እንዳይችል አንድ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል።፡ ይህን ችግር ለመፍታት ማህበረሰቡ ላገኘው አገልግሎት ደረሰኝ የመጠየቅ ባህሉ እንዲዳብር፣ ግብር ከፋዩም ግዴታውን በታማኝነት እንዲወጣ ቢሮው ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ በስፋት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ የገቢ ግብር ህግን ተላልፈው የሚገኙትን በተጨባጭ መረጃ በመያዝ ተጠያቂ የማድረግ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥል ገልጸዋል። "ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ልማትን ማጠናከሪያ ነው" ያሉት የሆሳዕና ከተማ ነዋሪ አቶ ደምሴ አዱኛ በበኩላቸው፣ በየዓመቱ የቤት ግብራቸውን በወቅቱና በታማኝነት እንደሚከፍሉ ተናግረዋል፡፡ ግብርን በወቅቱና በታማኝነት አለመክፈል እድገትን ወደኋላ እንደሚጎትት ጠቅሰው፣ በዘርፉ ይስተዋል የነበረው ህገወጥ አሰራር ለመከላከል የግብር አሰባሰብ ሥራውን ለማዘመን የተሰራው ሥራ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። በከተማው በልብስ ስፌት ሥራ ላይ የተሰማራችው ወይዘሪት ሰላማዊት ዮሴፍ በበኩሏ ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ልማትን ለማፋጠንና ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ ያግዛል ብላለች። ከከተማው የልማት ሥራዎች ተጠቃሚ በመሆኔ የሚጠበቅብኝን ግብር በወቅቱ በመክፈል ግዴታዬን እወጣለሁ ያለችው ወይዘሪት ሰላማዊት፣ ግብርን በወቅቱና በአግባቡ የመክፈል ባህል መጠናክር እንዳለበት ተናግረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ያሳድጋል
Oct 28, 2025 355
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ፋይዳው የጎላ መሆኑን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። በቅርቡ ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት ከሀይል አማራጭነት የዘለለ የተለያዩ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ከእነዚህ ጠቀሜታዎች መካከል አንዱ የኒኩሌር ህክምና አገልግሎት ይገኝበታል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መምህር፣ ሀኪም፣ ተመራማሪና የካንሰር ሕክምና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን ሁነኛው ለኢዜአ እንደገለፁት የኒኩሌር ፕላንቱ በሕክምናው ዘርፍ ለኢትዮጵያ ትልቅ እድል ይዞ የሚመጣ ነው። በተለይ በዋናነት የካንሰር በሽታን ለማከም ያለው ፋይዳ ላቅ ያለ በመሆኑ የህክምና አገልግሎቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደርሰዋል ብለዋል። አክለውም ለራዲዮ ቴራፒ ሕክምና የሚውሉ መድሀኒቶችን ለማምረትና የቆይታ ጊዜያቸው ከስምንት ቀን የማይበልጡ መድሀኒቶችን ብልሽት መፍታት ያስችላል ነው ያሉት። ከኒኩሌር ጋር በተያያዘ መንግስት የወሰደው ኢንሼቲቭ ከህክምና አገልግሎቱ ባለፈ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለው ፋይዳም ከፍተኛ በመሆኑ መበረታታት እንዳለበት ዶክተር ሰለሞን ተናግረዋል። ሌላው የዩኒቨርሲቲው መምህርና የህጻናት ካንሰር ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሙሉአለም ንጉሴ በበኩላቸው ያደጉ ሀገሮች የኒኩሌር ሕክምናን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠቀሙበት አንስተዋል። የኒኩሌር ሀይል ለአዋቂም ሆነ ለሕጻናት ሕክምና የበሽታውን ሁኔታና ያለበትን ደረጃ ለይቶ ለማከም ያለው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ለሕክምናው ዘርፍ ጭምር ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ብለዋል። የኒኩሌር ሀይል ለካንሰር ሕክምና አገልግሎት ሦስት ዋና ዋና ፋይዳ አለው ያሉት ባለሙያው የካንሰር አይነቱንና የስርጭቱን መጠን እንዲያውቅ ይረዳዋል ነው ያሉት። ሕመምተኛውም የበሽታው አይነትና ስርጭትን መሰረት ያደረገ ሕክምና እንዲያገኝ እንደሚያስችለው ገልጸዋል። ለካንሰር ሕሙማን የኒኩሌር ሕክምና በሀገር ውስጥ ስለማይሰጥ ሕክምናውን ለማግኘት ወደ ውጪ እንደሚላኩ የገለጹት ዶክተር ሙሉአለም በዚህም ምክንያት ለወጪና እንግልት ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል። የኒኩሌር ሕክምና ከሌሎቹ የሲቲ ስካን፣ ኤም አር አይ እና ሌሎች መሳሪያዎች አንጻር ያለውን በሽታ ለይቶ ማሳየት ብቻ ሳይሆን ያደረሰውን የጉዳት መጠን ጭምር ለይቶ የሚያሳይ ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ክብሩ ክፍሌ ናቸው። በካንሰር የተጠቃ የሰውነት አካል ምን ያህል እንደተጎዳ፣ የትኛው ክፍሉ ሥራውን በአግባቡ እያከናወነ እንደሚገኝ የሚለውን በትክክል መለየት የሚያስችል የዘመናዊ ሕክምና ትልቅ መሳሪያ መሆኑን አስረድተዋል። እንደ ሀገር ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሸጋግር በመሆኑ መንግስት የወሰደው ተነሳሽነት ሊበረታታና ሊደገፍ ይገባል ሲሉም ምሁራኑ ገልፀዋል።
በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተደረገው ሪፎርም በዘርፉ ከፍተኛ እድገት እንዲመዘገብ አድርጓል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Oct 28, 2025 88
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተደረገው ሪፎርም በዘርፉ ከፍተኛ እድገት እንዲመዘገብ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሄዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የ2025 የዲጂታል ቴክኖሎጂ አካታች የ2030 ስትራቴጂ በመጀመር በዘርፉ የተሻለ እድገት ለማስመዝገብ እየሰራች ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠና 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች ስልጠናውን በነጻ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ለውጡ በተጀመረበት ወቅት 37 ሚሊዮን የቴሌኮም ተጠቃሚዎች እንደነበሩ ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት ቁጥሩ 93 ሚሊዮን ደርሷል ነው ያሉት። ይህም ሪፎርም በዘርፉ ትልቅ እድገትና ለውጥ እንዲመዘገብ ማድረጉን አመላካች ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት 55 ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎች ዲጂታል ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በ2028 ዘርፉ 11 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ሃብት ያመጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል። ከዚሁ ዘርፍ 1 ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጠር የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህም 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደሚገኝ መተንበዩንም ነው የተናገሩት፡፡ በተለይ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍም ሰፋፊ ለውጥና ብቃት እየተመዘገበ መሆኑን አብራርተው፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ ከሚጠበቀው በላይ ስኬታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተካሔደው ሪፎርም ኢትዮጵያ በራሷ አቅም የዲጂታል ገበያ ላይም ስኬታማ ስራዎች እየሰራች መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 28, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ወቅት ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታላይዜሽንን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል ብለዋል። ይህ ትልቅ ቁጥር መሆኑን ጠቁመው 93 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ሲሆኑ 55 ሚሊዮን ዜጎች የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኢትዮጵያን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የጀመረነው ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን አመላካች ነው ሲሉክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል።
በደሴ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተዘጋጀ
Oct 28, 2025 76
ደሴ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ተደረገ። ማዕከሉ 16 ተቋማት እና ከ70 በላይ የአገልግሎት ዘርፎች የተመቻቹ ሲሆን፤ ይህም ብልሹ አሰራርን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንደሚሰጡ ተመላክቷል። ለአገልግሎት አሰጣጡ ምቹ እንዲሆን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የሲስተም ዝርጋታ ስራው የተሳካ ስለመሆኑ በተደረገው የሙከራ ትግበራ ማረጋገጥ ተችሏል። ለከተማው ማህበረሰብ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት በቅርብ ቀናት ወደ ተሟላ ስራ እንደሚገባ ተጠቁሟል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝን ጨምሮ ሌሎች የከተማ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከሉን ተመልክተዋል።
ስፖርት
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
Oct 29, 2025 45
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። አዲስ አዳጊው ነጌሌ አርሲ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከቀኑ 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ነጌሌ አርሲ በሊጉ እስከ አሁን ካደረጋቸው ጨዋታዎች በአንድ ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሊጉ ባደረገው አንድ ጨዋታ ሶስት ነጥብ በማግኘት አንድ ተስተካካይ መርሃ ግብር እየቀየረው ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ቡድኖቹ በሊጉ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሃዋሳ ከተማ ከወላይታ ድቻ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሃዋሳ ከተማ በሶስት ነጥብ ስምንተኛ፣ ወላይታ ድቻ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ቡድኖቹ በሁለተኛ ሳምንት ካስተናገዱት ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ምሽት 12 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሲዳማ ቡና በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ፋሲል ከነማ በአራት ነጥብ አራተኛ፣ ሲዳማ ቡና በስድስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ሲዳማ ቡና ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ዳግም ይረከባል። በሶስተኛ ሳምንት ኢትዮጵያ መድን ከሸገር ከተማ ሊያደርጉት የነበረው ጨዋታ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ከፒራሚድስ ጋር በሚያደርገው የሁለተኛ ዙር የመልስ ጨዋታ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።
በካራባኦ ዋንጫ ዛሬ ለሩብ ፍጻሜ ለማለፍ ወሳኝ ጨዋታዎች ይደረጋሉ
Oct 29, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ አራተኛ ዙር የሁለተኛ ቀን ውሎ አምስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ኒውካስትል ዩናይትድ ምሽት አምስት ላይ በሴንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም ቶተንሃም ሆትስፐርስን ያስተናግዳል። ኒውካስትል ዩናይትድ አምና በካራባኦ ዋንጫ ፍጻሜ ሊቨርፑልን በማሸነፍ ዋንጫውን ለመጀመሪያ ጊዜ ማንሳቱ የሚታወስ ነው። ቶተንሃም ሆትስፐርስ ውድድሩን አራት ጊዜ አሸንፏል። ኒውካስትል በሶስተኛው ዙር ብራድፎርድ ሲቲን፣ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ዶንካስተር ሮቨርስን አሸንፈዋል። በሌሎች መርሃ ግብሮች አርሰናል ከብራይተን፣ ሊቨርፑል ከክሪስታል ፓላስ፣ ስዊንሲ ሲቲ ከማንችስተር ሲቲ እና ዎልቭስ ከቼልሲ በተመሳሳይ 4 ሰዓት ከ45 ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ትናንት የተጀመረው የካራባኦ ዋንጫ የአራተኛ ዙር መርሃ ግብር ዛሬ በሚደረጉ ጨዋታዎች ይጠናቀቃል። ብሬንትፎርድ፣ ፉልሃም እና ካርዲፍ ሲቲ ለሩብ ፍጻሜ ያለፉ ክለቦች ናቸው። እ.አ.አ በ1960 የተጀመረው የካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ የእንግሊዝ ፉትቦል ሊግ ዋንጫ) በእንግሊዝ ከአንጋፋው ኤፍ ካፕ ውጪ የሚደረገው የጥሎ ማለፍ ውድድር ነው። ሊቨርፑል 10 ጊዜ ዋንጫውን በማንሳት የውድድሩ ስኬታማ ክለብ ነው። ማንችስተር ሲቲ ስምንት እና ማንችስተር ዩናይትድ ስድስት ጊዜ ውድድሩን በማሸነፍ ይከተላሉ።
መቻል ድል ቀንቶታል
Oct 28, 2025 96
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር መቻል ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 3 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መሐመድ አበራ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ዓለምብርሃን ይግዛው ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ዩጋንዳዊው ሳይመን ፒተር በፍጹም ቅጣት ምት ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ መቻል በሊጉ ሁለተኛ ድሉን ሲያስመዘግብ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ሽንፈቱን አስተናግዷል።
መቻል ድል ቀንቶታል
Oct 28, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር መቻል ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 3 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መሐመድ አበራ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ዓለምብርሃን ይግዛው ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ዩጋንዳዊው ሳይመን ፒተር በፍጹም ቅጣት ምት ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ መቻል በሊጉ ሁለተኛ ድሉን ሲያስመዘግብ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ሽንፈቱን አስተናግዷል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው
Oct 29, 2025 48
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚችል ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደርና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ አኒል ኩማር ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በብዝሃ የአየር ንብረት የታደለች፤ ልዩ ልዩ የተፈጥሮ ሀብቶችን የያዘች፣ በርካታ እፅዋቶችና የዱር እንስሳት ዝርያዎች የሚገኙባት መሆኗን አምባሳደሩ ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚችል ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ የአገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ ለብዝሃ ህይወት መጎልበት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ስራው አስደናቂ መሆኑን ተናግረዋል። በአፋር ክልል የሚገኘው ዝቅተኛው የደናክል በረሃ እና የተለየ የአየር ንብረት ያለው የስምጥ ሸለቆ መነሻ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ አረንጓዴ የሆኑና ከፍተኛ የዝናብ መጠን የሚያገኙ ደጋማ አካባቢዎችን የያዘች መሆኗንም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያሉ ልዩ ልዩ የአየር ንብረት ጸባዮች፣ የዕጽዋትና የዱር እንስሳት ዝርያዎች ሀገሪቱን ብዝሃ ተፈጥሮ የተቸራት አድርጓታል ብለዋል፡፡ ይህም የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስፋት ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አመላክተዋል፡፡ አምባሳደሩ በኢትዮጵያ የተተገበሩ እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ መርሃ-ግብሮችና ሰፋፊ የልማት ስራዎች ለሀገሪቱ የወደፊት ብልፅግና ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቅሰው ፤ የተተከሉት ዛፎች እንዲጸድቁ የሚደረገውን እንክብካቤ አድንቀዋል። በቀጣዩች አስር ዓመታት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደማሚ ለውጦችን ታስመዘግባለች ሲሉም ገልጸዋል። ህንድ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ለምታከናውነው ተግባር አድናቆት እንዳላት ጠቁመው፤ አገራቸው በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ አስፈላጊነት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ አቋም እንዳላት ተናግረዋል፡፡ ህንድ እና ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ የጋራ ስምምነት እንዳላቸው አስታውሰው፡ ትብብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ያከናወነቻቸው ተግባራት የአዕዋፋትንና የዱር እንስሳትን ስደት ትርጉም ባለው መልኩ መቀነሱ ይታወቃል፡፡
በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደናቂ የልማት ስኬት ማስመዝገብ ተችሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Oct 28, 2025 110
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደናቂ የልማት ስኬት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። በመደበኛ ስብሰባው ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምላሽና ማብራሪያቸው፤ 2017 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ የታሪክ እጥፋት ውስጥ ይቻላሉ ተብሎ የማይታሰቡ ጉዳዮች የተቻሉበት የስኬት ዓመት እንደነበር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ያነገባቸውን ዓላማዎችና ያስገኛቸውን ውጤቶች አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአንድ ዘርፍ ላይ ተንተርሶ ከድህነት ሊወጣ አይችልም በሚል ብዝኅ ዘርፍና ብዝኃ ተዋናይ የኢኮኖሚ አቅጣጫ ላይ የተነደፈው ፖሊሲ በእጅጉ ውጤታማ እየሆነ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎች ሳይዘነጉ አምስቱ ግንባር ቀደም የተሰናሰሉ በብዝኅ ዘርፍ ቢመሩ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እንደሚያሻሽሉ እምነት መጣሉን አስረድተዋል። ግብርና እና ማዕድን ለኢንዱስትሪ ግብዓት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ ኢንዱስትሪውም ግብርናን የሚያፋጥን ማሽን ፈጣሪ ነው ብለዋል። ቴክኖሎጂ የታከለበት ብዝኅ ዘርፍ የኢኮኖሚ ልማትም ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ያስቻለ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ እንደሚገኝ አንስተዋል። የብዝኅ ተዋናይነትም መንግስት አንድ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ በመሆን ከግሉ ዘርፍ፣ ከህዝብና የልማት አጋሮች ጋር ተሳስሮ የኢትዮጵያን ልማት በየፈርጁ ማፋጠን አለበት የሚል እምነት መያዙን ገልጸዋል። የግልና መንግስት አጋርነት እሳቤ ያለ ቢሆንም የመንግስትና ህዝብ አጋርነት ግን ግልጽ አቅጣጫ የተቀመጠለት ከለውጡ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በመንግስት የህዝብ አጋርነት ኢትዮጵያ በርካታ ስኬቶች ማስመዝገቧን ጠቅሰው፤ ለዚህም የአረንጓዴ አሻራ 48 ቢሊየን ችግኞች ስኬት ማሳያ ነው ብለዋል። እያንዳንዱ ችግኝ ከጅምሩ እስከ ተከላ መርሃ ግብሩ ባለው ሂደት አንድ ዶላር ቢወስድ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ 48 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስት ማድረግ መቻሏን አስረድተዋል። በዚህም ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ያለመታከት ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን በመስጠት በየዓመቱ ስለሰሩ ይህን ያክል ሃብት ያስወጣ የነበረን ስራ በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር ማሳካት ተችሏል ብለዋል። በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ የሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለቀጣናው ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ልማት እንዲሁም ለጋራ ብልፅግና መሪ ሚና እየተወጣች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Oct 27, 2025 163
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 17/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለቀጣናው ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ልማት እንዲሁም ለጋራ ብልፅግና መሪ ሚና እየተወጣች ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 2ኛውን የኢትዮጵያ የውሃ እና ኢነርጂ ሳምንት በሳይንስ ሙዚየም አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል፣ ለውሃ እና ለአረንጓዴ ልማት በሰጠችው ትኩረት ለውጥ እያመጣች ሚሊዮኖችን ተጠቃሚ እያደረገች መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የቀጣናው የኃይል ማዕከል እየሆነች ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለጂቡቲ፣ ለሱዳንና ለኬንያ ታዳሽ ኃይል እያቀረበች ነው ብለዋል። በቅርቡም ወደ ሌሎች ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እንደምትልክ ጠቅሰው፥ ይህም የጋራ ቀጣናዊ የብልጽግና ራዕይዋ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዚህ የላቀ ራዕይ ምሰሶ እንደሆነ ገልጸው፥ ግድቡ ጽናታችንን፣ አንድነታችንንና በአፍሪካ መጻኢ የጋራ ህልሞች ላይ ያለንን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል። የግድቡ አገልግሎት ከኃይል ልማት ባሻገር ለብዝኃ ህይወት ጥበቃ፣ ጎርፍን ለመከላከልና በታችኛው ተፋሰስ ላሉ ሀገራት የተስተካከለ የውሃ ፍሰት እንዲያገኙ ያስችላል ነው ያሉት። ከፉክክር ይልቅ የጋራ ተጠቃሚነትንና ትብብርን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን በማንሳትም፥ ኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞቿ የቀጣናው የትስስር መሠረቶች ናቸው በሚል ግልፅ አቋም እየሠራች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም በአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ ግብር ባለፉት ዓመታት ከተተከሉ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች አንድ ሦስተኛ ያህሉ በዓባይ ተፋሰስ መተከላቸውንና ይህም ለሌሎች ሀገራት ፋይዳው የላቀ መሆኑን አስረድተዋል። በሌላ በኩል ኢኮኖሚያችን እያደገ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የባህር በር ማግኘት ለቀጣይ እጣፈንታችን ዋስትና የሚሰጥ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የባህር በር ለኢትዮጵያ የግድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የባህር በር ማግኘት ንግድን ለማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ውህደትን ለማጎልበትና ቀጣናዊ ትብብርን ለማሳደግ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር እጣፈንታዋ የተሳሰረ በመሆኑ በጋራ ለመልማት እና ዘላቂ ጥቅምን ለማስጠበቅ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት እየሠራች ነው ብለዋል። አፍሪካ ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ዋስትናዋን እንድታረጋግጥ ኢትዮጵያ መሪ ሚናዋን መወጣቷን እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል።
እምቦጭን በዘላቂነት ለመከላከል የህብረተሰብ ተኮር ሥራ ውጤት እያስገኘ ነው
Oct 26, 2025 198
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፡-እምቦጭን በዘላቂነት ለመከላከል የህብረተሰብ ተኮር ሥራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ ሞቱማ መቃሳ ገለጹ፡፡ በውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ ሞቱማ መቃሳ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ያቀደቻቸውን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች ለማከናወን የውኃ ሀብቷን መጠበቅ ወሳኝ ነው። ስለሆነም መንግስት በአገሪቷ የልማት እቅዶች ውስጥ የውኃ አስተዳደርና ጥበቃን ቅድሚያ ሰጥቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ለአብነትም በአገሪቷ ውስጥ ምን ያህል የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውኃ ሀብት እንዳለ በትክክል የመለየትና የመመዝገብ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህን ሀብት ለየትኞቹ የልማት ዘርፎች በምን ያህል መጠንና ጥራት ለማዋል እንደሚቻል የውኃ አቅም ልየታ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የውኃ ሀብት አስተዳደርና ጥበቃ ስራ ከፍ ብሎ እንዲመራ ሚኒስቴሩ መዋቅራዊ ማሻሻያ ማድረጉንም አመልክተዋል። ከፍተኛ ትኩረት ከሚሹ የውኃ አካላት ጥበቃ ጉዳዮች መካከል አንዱ በእምቦጭ አረም ምክንያት የሚከሰተውን ችግር ማቃላል መሆኑን አመልክተዋል። እምቦጭ በፍጥነት የሚስፋፋና በየጊዜው ተመልሶ የሚመጣ መሆኑን ያወሱት አቶ ሞቱማ፤ በዘላቂነት ለማቃለል በየጊዜው አስቸጋሪ ፈተና መሆኑን አንስተዋል። ይህንን ችግር መፍትሄ ለመስጠት ሚኒስቴሩ በትኩረት እየሰራበት እንደሚገኝም አብራርተዋል። ይህን ዘላቂ ችግር ለማቃለል ህብረተሰብን ያማከለ አሰራር ተቀይሶ በመተግበር ላይ እንደሚገኝና ውጤትም እየተገኘበት እንደሆነም አስታውቀዋል። በጣና ሐይቅና በሌሎች የውኃ አካላት ላይ የእምቦጭ አረምን ችግር ለመፍታት ከተጀመሩ ሥራዎች በተጨማሪ ህብረተሰብ ተኮር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ሞቱማ ተናግረዋል። የውኃ ሀብት ጥበቃና አስተዳደር የሀገር ጉዳይ በመሆኑ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና መላው ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Oct 24, 2025 293
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀመረ
Oct 24, 2025 204
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦11ኛው የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተሞች በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው። በፎረሙ ላይ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች ምክክር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በቀጣናው መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከል የተጀመሩ የቅንጅት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኢጋድ
Oct 20, 2025 404
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኢጋድ ሶስተኛው የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ በኬንያ ናይሮቢ ተጀምሯል። “በኢጋድ ቀጣና ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሰራተኛ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር ህጋዊ ማዕቀፍን ማሻሻል” የስብሰባው መሪ ቃል ነው። በስብሰባው ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት የሰራተኛ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች፣ ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(አይኤልኦ)፣ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(አይኦኤም)፣ የአውሮፓ ህብረትና የልማት አጋሮች ተገኝተዋል። በኢጋድ ቀጣና የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በቀይ ባህር መስመር ያለውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ከኢጋድ ቀጣና ውጪ የሚገኙ ዜጎች አባል ሀገራትን በነጠላ የመግቢያ ቪዛ መጎብኘት የሚያስችላቸውን የቪዛ ኢኒሼቲቭ ይፋ ይደረጋል። ኢኒሼቲቩ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርና ድንበር ተሻጋሪ ንግድን ማሳለጥ እንዲሁም ቱሪዝምን የማሳደግ ፋይዳ እንዳለው ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአውሮፓ ህብረት የፋይናንስ ድጋፍ የሚተገበረው ነጻ የሰዎችና የቁም እንስሳት እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፍ ሁለተኛ ምዕራፍ ይፋ ይሆናል። ማዕቀፉ ህጋዊ የፍልሰት መንገዶች ለማጠናከር እና ቀጣናዊ ትስስርን የማሳካት ግብ ያለው መሆኑንም አመልክቷል። ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሰንሰለትን መበጣጠስ፣ በፍልሰት በሌላ ሀገር የሚገኙ ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ላይ ምክክር ያደርጋሉ። በውይይቱ ማብቂያ ሀገራት የጋራ መግለጫ እንደሚያወጡ የሚጠበቅ ሲሆን ደህንነቱ የተጠበቀ መደበኛ ፍልሰት፣ ጠንካራ የሰራተኛ አስተዳደር ስርዓት መፍጠርና ለሰዎች ዝውውር የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ መስጠት ላይ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እንደሚገልጹ ተጠቁሟል። ኢጋድ በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የጋራ ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክቷል። ዜጎች ህጋዊ አማራጮችን እንዲከተሉና የኢኮኖሚ ፈተናን ጨምሮ ለሌሎች ገፊ ምክንያቶች ዘላቂ መፍትሄ መስጠት በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ ገልጿል። ስብሰባው ጥቅምት 10 እና 11 በባለሙያዎች፣ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚኒስትሮች ደረጃ ይካሄዳል።
የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በቁርጠኝነት ሊተገብሩ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት
Oct 19, 2025 398
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) አፈጻጸም ውጤታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብስባ ከጥቅምት 11 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገም እና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስ እና ዘላቂ የውሃና ተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚከናውን ኢዜአ ከህብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
የብዙዎች ቤት…
Oct 27, 2025 168
እስካሁን በተደረገ የጥናት ውጤት መሠረት ከ81 በላይ የአጥቢ እንስሣት፣ ከ450 በላይ የአዕዋፍ እና ከ400 በላይ የእፅዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው። ከእነዚህ መካከል አምስቱ የአዕዋፍ ዝርያዎች በዚህ ሥፍራ ብቻ ይገኛሉ፤ ከአምስቱ መካከል በተለይም የአንዷ ዝርያ ዓለም አቀፍ የዘርፉ ተመራማሪዎችንና ጎብኚዎች ቀልብ መሳቡ ይጠቀሳል። ከአካባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ጋር መጣጣም የቻሉ የቆላ እፅዋት (ዛፎች) በምቾት በስፋት እንደሚገኙበትም ይገለጻል። የተመሠረተው በ1958 ዓ.ም ሲሆን፤ ስፉቱም 591 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው፤ በቁጥርም ሆነ በሥብጥር የብዙዎች መኖሪያ የሆነው ይህ ሥፍራ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ይሰኛል። መንግሥት በሰጠው ትኩረት ከነበረው በተሻለ ሁኔታ እንስሣቱም ሆኑ እፅዋቱ እየኖሩ ነው፤ ከሕገ ወጥ ድርጊትም እንዲጠበቁ ማድረግ መቻሉን የፓርኩ ኃላፊ አደም መሐመድ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በፓርኩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁንም ለ247 ወገኖች ቋሚ እና ለ2 ሺህ 535 ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ዓመትም በ1 ሺህ 751 የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንደተጎበኘ ኃላፊው ገልጸዋል።
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 679
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 658
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 867
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1460
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1977
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2817
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2942
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 755
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 557
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6397
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4876
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
''ቦር ተራራ'' የየሞች የፈውስ ምድር
Oct 27, 2025 225
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) የም ዞን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ይገኛል። በዞኑ የቦር ተራራ ዋነኛው የመድኃኒት እጽዋት መገኛ እና ምንጭ በመሆኑ የሞች በየዓመቱ ጥቅምት ወርን ጠብቀው በ17ኛው ቀን ከዚህ ተራራ በህብር ሆነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስነ-ስርዓት ያካሂዳሉ፤ ይሰባስባሉም ። የቀደምት የየም አባቶችና እናቶችን በማሳተፍ የሚከወነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ከባህር ጠለል በላይ 2 ሺህ 939 ሜትር ከፍታ ላይ በሚገኘው ቦር ተራራ ላይ ነው። በዚህ ተራራ ላይ በየዓመቱ ጥቅምት 17 ቀን የሞች ለዓመት የሚያገለግላቸውን የመድኃኒት እጽዋት ይለቅማሉ። ተግባሩንም አዋቂዎች በጋራ ሰብሰብ ብለው ለመድኃኒት የሚውለውን ቅጠል በጥሰው፣ ስር ምሰው፣ አስሰውና መርጠው ይሰበስባሉ። ይህም የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስርዓት "ሳሞ ኤታ" ተብሎ ይጠራል ። አያምጣውና ህመም ሲከሰት ታማሚውን ሰው ወይም እንስሳን ከበሽታው ለመፈወስ የተዘጋጀው ባህላዊ መድሃኒት በባህላዊ ሃኪም ትዕዛዝ መሰረት በህመሙ ልክ ይታዘዝለታል። መድሃኒቱን ለመጠቀምም የጠቢባን አባቶችን ፈለግ ተከትሎ መፈፀም የግድ ይላል። የሞች አጅግ አስገራሚ እና አስደናቂ የሆኑ የበርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤት ናቸው ካስባሏቸው እሴቶች መካከል ይህ ለየት ያለው ክዋኔያቸው አንዱ ነው፡፡ አባቶች ታዳጊና ወጣቶችን አስከትለው ወደ ቦር ተራራ በመውጣት የሚፈፅሙት ባህላዊ ክዋኔ በመሆኑም ከትውልድ ወደ ትውልድ ቅብብሎሹን ጠብቆ እስከ አሁን እንዲዘልቅ እድርገውታል። በየሞች ዘንድ የባህላዊ መድኃኒት አዋቂዎች ከሚባሉት መካከል አንዱ አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም፤ የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ልምድን የቀሰሙት ከአባታቸው መሆኑን በመግለፅ አያታቸው ከቅድመ አያቶቻቸው በመውረስ እዚህ እንዳደረሱት ይናገራሉ። የቦር ተራራ ለመድሃኒት ዕፅዋት ለቀማው የተመረጠበትን ምክንያት ሲያስረዱም ቦታው ተራራ በመሆኑ ማንም ያልደረሰባቸው የተለያዩ እፅዋትን ለማግኘት አመቺ ከመሆኑ ጋር ያያይዙታል። በሌላም በኩል ጠዋት ፀሐይ ስትወጣ መጀመሪያ የምታገኘው ተራራውን በመሆኑና ክረምቱ አልፎ ጥቅምት ሲገባ የተለያዩ ቅጠላ ቅጠሎችን በብዛት እና በዓይነት ለማግኘት ተመራጭ ወቅት መሆኑም ቦታው የተመረጠበት ሌላኛው ምክንያት ነው ብለዋል። በጥቅምት 17 ለመድኃኒትነት የሚያገለግለው ዕፅዋት ቅጠልም በየፈርጁ ተለቅሞ እና ተቀምሞ ይቀመጣል ሲሉም አስረድተዋል። የተዘጋጀው ባህላዊ መድኃኒትም ለሰው ልጆችና ለቤት እንስሳት ያገለግላል ሲሉም አስረድተዋል፡፡ ይኸው በዚህ ቀን የተለቀመው የመድኃኒት ዕፅዋት ከዚህኛው ጥቅምት 17 እስከሚቀጥለው ዓመት ጥቅምት 17 ድረስ እንደሚያገለግልም አቶ ጌታቸው አስረድተዋል፡፡ የባህል መድኃኒት ሰብሳቢዎች እና ተጠቃሚዎች ጊዜውን ጠብቀው ከተለያዩ ቦታዎች ወደ ቦር ተራራ እንደሚመጡ የሚገልጹት የባህል መድኃኒት አዋቂው ዛሬ ዛሬ እሳቸውን ጨምሮ መድኃኒት ቤቶችን በመክፈት ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ የባህል መድኃኒቶችን በመሸጥ ኑሯቸውን እየመሩ የሚገኙ አያሌ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉም ይናገራሉ። ሌላኛው የባህል መድኃኒት አዋቂው አቶ ወልደመስቀል ጆርጋ በበኩላቸው በየሞች ዘንድ የተዘጋጀው የመድኃኒት ዕፅዋት ጥቅም ላይ የሚውለው ህመም ሲያጋጥም ብቻ ሳይሆን በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል መሆኑን ጠቁመው መድኃኒቶቹም ብቻቸውን እንዲሁም ከምግብ ጋር በመመገብ ለጥቅም እንደሚውሉም አንስተዋል። የየም ምድር የበርካታ የመድኃኒት ዕፅዋቶች መገኛ አካባቢ " የፈውስ ምድር " ነው የሚሉት ደግሞ በየም ባህላዊ መድኃኒት ዙሪያ ጥናት ያደረጉት በጅማ ዩኒቨርሲቲ የፎክሎር መምህር እና ተመራማሪ ለማ ንጋቱ (ዶ/ር) ናቸው። ከየሞች አያሌ የባህል ዕሴቶች መካከል የባህል መድኃኒት ለቀማና ቅመማ አንዱና ዋነኛው የሀገር በቀል እውቀት ማሳያ መሆኑን ገልፀው የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ስነ-ስርዓቱ ከጥንት ጀምሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ዛሬ ላይ የደረሰ እንደሆነም ያስረዳሉ፡፡ ማህበረሰቡ የራሱንም ሆነ የእንስሳትን ጤና የመጠበቅ የቆየ ባህል ያለው መሆኑን በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው የባህላዊ መድኃኒት ለቀማው ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚሳተፉበት ዓመታዊ ክዋኔ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ሌላው ገራሚው ነገር ይላሉ አጥኚው ታላላቆች ታናናሾቻቸውን አስከትለው የለቀማ ሂደቱን የሚያስረዱበት መንገድ ደግሞ ስርዓቱ ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፍ የሚያስችል ትውልድ ተሻጋሪ የሀገር በቀል እውቀት ሽግግር ስርዓት ማሳያ እንደሆነም ነው የገለጹት። በዚህም ሂደት የሚነገሩ ስነ-ቃሎች መሞጋገስ፣ ጭፈራና ደስታ ይስተናገድባቸዋል። ይህም ማህበራዊ ትስስርን ይበልጥ የሚጠናክሩበትን ሁነት የሚፈጥር ስርዓት ነው። የየም ዞን ባህል እና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ሞጋ በበኩላቸው የቦር ተራራ የመጀመሪያውን የማለዳ የፀሐይ ጎህ የሚፈነጥቅበት የንጋት ብርሃን ቀድሞ የሚያገኝ በመሆኑ፥ በዚህ አካባቢ የሚገኙ እጽዋት በሽታን የመከላከልና ፈዋሽነታቸው ከፍተኛ ነው ተብሎ ስለሚታመን ለዚህ ክዋኔ ቦታው መመረጡን ነው የሚገልፁት። ለዚህም ነው የሞች ይህንን ስፍራ ከሌሎች ቦታዎች አስበልጠው የሚወዱት፤ በየዓመቱም ጥቅምት 17 ቀን ወደ እዚህ ስፍራ በማቅናት ለዓመት ፍጆታ የሚያገለግላቸውን መድኃኒትም ይሰበስቡበታል ብለዋል። ጥቅምት 17 በየም ዘንድ ለየት የሚያደርገው ሌላው የመድሃኒት ዕፅዋት ለመልቀም እና ለመጠቀም ብቻ ሳይሆን የለቀማውን ትዕይንት ለመመልከት የሚመጡ ቱሪስቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸው ሌላው ትልቁ ትሩፋት ነው ይላሉ። የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማው ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት በመሆኑ፥ ለአብሮነት እና ሃገር በቀል እውቀት ለመቅሰም ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ነው አቶ መስፍን የገለፁት።
የአፍሪካ የግብርና፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ፤ እድሎች እና ፈተናዎች
Oct 20, 2025 500
አፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማሳካትና እንድትበለጽግ የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ መዕራፍ ላይ ይገኛል። የአህጉሪቱን የመለወጥ ትልም ባሏት እምቅ ተፈጥሯዊ ጸጋዎች ላይ የተመረኮዘ ነው። ተዝቆ የማያልቀው የአፍሪካ ብዝሃ ሀብት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግና አይበገሬ አቅም መገባንት የሚያስችሏትም ጭምር ናቸው። ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ ሀብቶቿ እና ብዝሃ ከባቢ የአየር ንብረቷ ከሀብቶቿ መካከል ይጠቀሳሉ። ግብርና አሁንም የአፍሪካ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው። ዘርፉ ለአህጉሪቱ 35 በመቶ የሚጠጋ አጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት(ጂዲፒ) አስተዋጽኦ ያደርጋል። 60 በመቶ ህዝብም በግብርና ስራ እንደሚተዳደር የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) ሰነድ ያሳያል። ከዚህም ውስጥ አብዛኞቹ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። ሴቶች በግብርናው ዘርፍ ካለው የሰው ኃይል የ50 በመቶ ድርሻው ይወስዳሉ። የአፍሪካ ህዝብ 60 በመቶ ድርሻ የያዘው ወጣት በግብርና ንግድ፣ እሴት መጨመርና የኢኖቬሽን ስራዎች ያለው ተሳትፎ እያደገ መጥቷል። የዓለም 60 በመቶ ያልለማ መሬት ያለው በአፍሪካ ነው። ሰፊ የውሃ ሀብቶችና እያደገ ያመጣው ብሉ ኢኮኖሚ(የባህር እና ሌሎች የውሃ ሀብቶች) ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ እድገትን የሚያረጋግጡ ናቸው። የመሰረተ ልማቶች ተደራሽነት ማደግ፣ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችና ኢኖቬሽንን የተመረኮዙ የፋይናንስ አማራጮችን መስፋት ግብርናን የምግብ ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለኢንዱስትሪ ልማት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ እና ንግድ መሳለጥ ትልቅ አቅም መሆን ይችላል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በግብርና ምርቶችና አገልግሎቶች ያለውን አህጉራዊ የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ በማሳደግ ረገድ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ ነው። የንግድ ቀጣናውን በሚገባ መጠቀም ከተቻለ እ.አ.አ በ2030 የግብርና ንግድ ልውውጡን በ30 በመቶ ማሳደግ እንደሚቻል ጥናቶች ያመለክታሉ። ግብርናው የተጠቀሱት ጥንካሬዎች ያሉት ቢሆንም ረጅም ጊዜ የዘለቁ መዋቅራዊ ፈተናዎች አብረውት ዘልቀዋል። የግብርና ምርቶች ላይ የሚፈለገውን ያህል እሴት አለመጨመር፣ የቴክኖሎጂ አጠቀቃምና የምርታማነት ውስንነት፣ የመሰረተ ልማቶች እና ሎጅስቲክስ በበቂ ሁኔታ አለመሟላት፣ ተቋማዊና አስተዳደራዊ ክፍተቶች ከአየር ንብረት ለውጥና ሌሎች ተፈጥሯዊ አደጋዎች እንዲሁም እያደገ ከመጣው ህዝብ ጋር ተዳምሮ ግብርናውን እየፈተነው ይገኛል። ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ማጠንጠኛ የሆነው ጉዳይ የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት(ካዳፕ) ነው። እ.አ.አ በ2003 የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ ባደረገው ስብሰባ የግብርና የምግብ ዋስትና ድንጋጌን አጽድቋል። ይህ ማዕቀፍ የማፑቶ ድንጋጌ ስያሜን በማግኘት የካዳፕ ትግበራ በይፋ እንዲጀመር አድርጓል። የማፑቶ ድንጋጌ እ.አ.አ በ2014 በማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025 የተተገበረ) በአዲስ መልክ የታደሰ ሲሆን የተለያዩ ቃል ኪዳኖችን በውስጡ ይዟል። ይህም በካዳፕ አማካኝነት የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ከአጠቃላይ ዓመታዊ ጥቅል ምርታቸው(ጂዲፒ) ቢያንስ ስድስት በመቶውን ለግብርናው ዘርፍ እንደሚመድቡና በየሀገራቱ በዘርፉ በየዓመቱ በአማካይ ስድስት በመቶ እድገትን የማሳካት ግብ አለው። ረሃብን ማጥፋት፣ ድህነትን በግማሽ መቀነስ፣ የማይበገር አቅም መገንባትና የጋራ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ሌሎች ግቦች ናቸው። ካዳፕ የአፍሪካ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ያላቸውን ኢንቨስተመንት በማሳደግ፣ በአፍሪካ የእርስ በእርስ የግብርና ንግድን በማሳደግና የፖሊሲ መሰናሰልን በመፍጠር ቁልፍ ሚና ተወጥቷል። ይሁንና የተመዘገቡት ውጤቶች ያልተመጣጠነ ልዩነት የሚታይባቸው ናቸው። የ2023 የካዳፕ የግምገማ ሪፖርት እንደሚያሳየው የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የማላቦ ግቦችን ማሳደግ የሚያስችል መንገድ ላይ እንዳልሆኑ ያስቀምጣል። ይሁንና 26 ሀገራት በተቀመጡ ግቦች መመዘኛ መሻሻል እንዳሳዩ ይገልጻል። ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ካሜሮን፣ ግብጽ፣ ማሊ፣ ጋና እና ጋምቢያ የተሻለ አፈጻጸም ካላቸው ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ። አብዛኞቹ ሀገራት በግብርና ኢንቨስትመንት፣ ምርታማነት እና የፖሊሲ ትግበራ ላይ ፈተናዎች እንዳሉበት ሪፖርቱ አመልክቷል። ሀገራት የሰነዱን ትግበራ ማፋጠንና ተቋማዊ ቅንጅትን ማጠናከር እንደሚገባቸው አሳስቧል። የማላቦ ድንጋጌ ወደ መገባደዱ ላይ የሚገኝ ሲሆን የካዳፕ ቀጣዩ ምዕራፍ የካምፓላ ድንጋጌ ነው። ይህ የትግበራ ምዕራፍ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚቆይ ነው። የካምፓላ ድንጋጌ ከማፑቶ እና ማላቦ ድንጋጌዎች ትምህርቶችን በመውሰድ የግብናውን እድገት ማላቅ ግቡ አድርጎ ይዟል። የካምፓላ አጀንዳ ኢኖቬሽን፣ ዲጂታላይዜሽን፣ አረንጓዴ እድገት እና አይበገሬነት ያላቸውን ሚና በማንሳት መስኮቹ ስርዓተ ምግብን ዘላቂና አካታች የማድረግ ግብን ማሳካት እንደሚያስችሉ አመልክቷል። በዚህ ማዕቀፍ እ.አ.አ 2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ህዝብ ይኖራታል ተብሎ የሚጠበቀውን አፍሪካን በራስ አቅም የመመገብ ውጥን የያዘ ነው። ይሁንና የግብርና ምርታማነት ከዓለም አቀፍ አማካይ የምርታማነት ምጣኔ አንጻር ሲታይ አሁንም ወደ ኋላ ቀረት ያለ ነው። ይህም አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች የተገደበ የፋይናንስ አቅርቦት ማግኘታቸው እንዲሁም የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትና የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው አለመደረጉ የችግሩ አብይ መንስኤ ሆኖ ይጠቀሳል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎችና የከባቢ አየር ብክለት ፈተናዎቹ እንዲበረቱ አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ የበይነ መንግስታት ፓናል(IPCC) አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እርምጃዎችን በፍጥነት ካልወሰደች እ.አ.አ በ2050 የግብርና ምርታማነቷ ከ20 እስከ 30 በመቶ ሊቀንስ እንደሚችል ገምቷል። ከ250 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ አፍሪካውያን ደህንነቱ ያልተረጋገጠ እና ንጽህናው ያልተጠበቀ የውሃ አቅርቦት ፈተና ውስጥ ይገኛሉ። በህዝብ ቁጥር መጨመር፣ በከተሜነትና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ምክንያት ንጹህ የውሃ አቅርቦትን የማግኘት ጉዳይ የበለጠ ሊስፋ እንደሚችል ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩና ፈተናዎች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ለአባል ሀገራት የፋይናንስ እና የቴክኒክ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል። የህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር የስራ ክፍሉ(DARBE) አማካኝነት የአፍሪካን ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞችና ኢኒሼቲቮች የተናበቡና የጋራ ግብ ያላቸው እንዲሆኑ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል። የአቅም ግንባታ፣ የቴክኒክ እና የፖሊሲ ድጋፍም የሚያደርግ ሲሆን ብሄራዊ እቅዶች ከአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሰነዶችና የአጋርነት ማዕቀፎች ጋር የተጣጠሙ መሆናቸውን ያረጋገጣል። የስራ ክፍሉ ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች ጋር አጋርነቶችን የማጠናከር ስራ ያከናውናል። ግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት እንዲሁም የተፈጥሮ እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በዘላቂነት መጠቀም ላይ የተቀናጁ አሰራሮችን መፍጠር ላይም ይሰራል። የዘርፉ አጠቃላይ ስራዎች አካል የሆነው ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎችና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገምና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም(ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ(ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስና ዘላቂ የውሃና የተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩም ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚያከናውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። አፍሪካ ወደ ዘላቂ ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር እና አካባቢ ጥበቃ እያደረገች ያለው ጉዞ አንገብጋቢ አጀንዳና ሽግግሩን ለማፋጠን ወሳኝ ሚና አለው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የፋይናንስ ማነቆ፣ መሰረተ ልማቶች እና የፖሊሲ የመፈጸም አቅም ውስንነትን ጨምሮ የተለያዩ ፈተናዎች ቢኖሩባትም እድሎቿ ፈርጀ ብዙ ናቸው። በርካታ ያልለማ መሬት፣ ሰፊ የውሃ ሀብት፣ ወጣቶች እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በአፍሪካ ዘላቂ የግብርና እድገት ለማረጋገጥና ሁሉን አቀፍ ስርዓተ ምግብ ለመገንባት የሚያስችል ነው። ለአርሶ አደሮች በቂ የፋይናንስ አቅርቦት ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ አቅማቸውን መገንባት ቁልፍ ጉዳይ ነው። ሀገራት ብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸውን ከአህጉራዊ ማዕቀፎች ጋር ማጣጣም ይኖርባቸዋል። ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ይገባል። የተፈጥሮ ሀብትን በሚገባ መጠቀም፣ በኢኖቬሽን ላይ መዋዕለ ንዋይን ፈሰስ ማድረግና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች፣ አረንጓዴ እና የበለጸገች አህጉር መገንባት ይቻላል።