ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ለብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ወደ ክልሉ የሚመጡ እንግዶች የተለያዩ መስኅቦችን ይጎበኛሉ
Nov 17, 2025 19
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡- ለ20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን አከባበር ወደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሚመጡ እንግዶች የቱሪዝም መስኅቦችን ለማስጎብኘት ዝግጅት ተደርጓል። ቀኑ በክልሉ መከበሩ ተፈሯዊ፤ ታሪካዊና ባህላዊ የቱሪዝም መስኅቦች ለማስተዋወቅ እንደሚጠቅም የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትልና የቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ መሐመድኑሪ ሳልያ ተናግረዋል። በዚህም መሠረት እንግዶች ሲመጡ በቀላሉ እንዲጎበኟቸው ዋና ዋና የቱሪዝም መስኅቦች ተለይተው በቂ ዝግጅት መደረጉን ለኢዜአ አረጋግጠዋል። የተለዩት መዳረሻዎችም፤ ጥያ ዓለም አቀፍ መካነ ቅርስ፣ ምድረ ከብድ አቦ ገዳም፣ የስልጤ ሙዚየም፣ ሀረ ሸይጣን ሐይቅ፣ አርቶ ፍል ውኃ፣ ሴራ ፌስቲቫል፣ መጨፈራ ሐይቅ፣ ወገና የከብቶች ቆጠራ ሥርዓት፣ ሃምበርቾ 777 ኢኮ ቱሪዝም እና ሶዲቾ ዋሻ መሆናቸውን ገልጸዋል። እንዲሁም አጆራ ፏፏቴ፣ ጀፎር፣ ጊቤ ሸለቆ ብሔራዊ ፓርክ፣ ብርብርሳ ፏፏቴ፣ ጥቅምት 17 ባህላዊ የመድኃት ለቀማ የሚከናወንበት ስፍራ (ሳሞ ኤታ)፣ኦሞ ሰው ሠራሸ ሐይቅ፣ መሪሾ ፌስቲቫል፣ ዘቢሞላ ሀድራ፣ ደቀንሽ ሞላ ፏፏቴ፣ ራጋ ማጋ የግጭት አፈታት ሥርዓት እና ፋቃ ከንፈልቻ ዋሻ በእንግዶች እንዲጎበኙ የተለዩ መስኅቦች መሆናቸውን ተናግረዋል። በተጨማሪም የባህል ምግቦችና አለባበስን እንግዶች በሚያልፉበትና በሚያርፉበት ለማስተዋወቅ ትኩረት መሰጠቱን አስታውቀዋል። ሆቴሎችና የእንግዳ ማረፊያዎችን ጨምሮ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በክልሉ የእንግዳ ተቀባይነት ባህል እንግዶችን ለመቀበል መዘጋጀታቸውን አቶ መሐመድኑሪ አረጋግጠዋል።
ጤናማ አመጋገብ ሲባል ምን ማለት ነው?
Nov 17, 2025 46
በፈረንጆቹ 2024 የዓለም እርሻና ምግብ ድርጅት እና የዓለም ጤና ድርጅት ባወጡት መመሪያ መሠረት ጤናማ ምግብ አራት መሠረታዊ መርሆዎችን ይይዛል። እነሱም፤ በቂ መሆን፣ ሚዛንን መጠበቅ፣ ልከኝነት እና የተሰባጠረ መሆናቸውን የሥርዓተ-ምግብ፣ የአካባቢ ጤናና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ተመራማሪ ዳዊት ዓለማየሁ ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህም መሠረት፡- በቂ መሆን፦ ሁሉንም አስፈላጊ ንጥረ ነገሮችና እነሱን የያዙ የምግብ መደቦች በበቂ መጠን እንዲሁም ከፍላጎት በላይ ሳይሆን ማቅረብ ማለት ነው። በዚህም የአመጋገብ ፍላጎቶችን ከዕድሜ፣ ጾታ፣ የእንቅስቃሴ ደረጃ እና የፊዚዮሎጂ ሁኔታ ጋር ማመጣጠን አስፈላጊ ስለመሆኑ አስረድተዋል። ሚዛንን መጠበቅ፡- ማክሮኒዩትሬንቶች (ፕሮቲን፣ ስብና ካርቦሃይድሬት) እድገት፣ ጉልበትና አጠቃላይ ጤናን በሚደግፍ መጠን መወሰድ አለባቸው ብለዋል። ልከኝነት፡- ከጤና አደጋዎች ጋር የተገናኙ ንጥረ ነገሮች እንደ ስኳር፣ ሶዲየም (ጨው)፣ የሳቹሬትድ ፋት (ጠጣር ስብ) እና ትራንስ ፋት (ተፈጥሯዊ ባሕርይው በፋብሪካ የተቀየረ ስብ) በተጠበቀ ገደብ ውስጥ መሆን አለበት ማለት ነው። ይህም ለህመም ተጋላጭነትን ለመቀነስ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስብጥር፡- የተለያዩ የምግብ ዓይነቶችን በተመጣጠነ ሁኔታ ማካተት በቂ ንጥረ ነገሮችን ለማግኘት ከማስቻሉ በላይ የምግብ እጥረትን ለመከላከል ይረዳል ብለዋል። የተሰባጠረ አመጋገብ ማለት በአንድ ገበታ በአንድ ጊዜ ቢያንስ አራት የምግብ ምድብ እንዲሁም በቀን ስድስት የተለያየ የምግብ ምድብ የያዘ ማለት ነው። የኢትዮጵያ ምግብን-መሰረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ ስድስት የምግብ መደቦች መያዙን አብራርተዋል። በዚህም መሠረት፡- 1ኛ. እህልና ሥራሥር (እንጀራ፣ ዳቦ፣ ቆጮ እና ቆሎ)፣ 2ኛ. ጥራጥሬ (አተር፣ ምስር፣ ሽምብራ እና ባቄላ)፣ 3ኛ. ለውዝ እና የቅባት እህል (ለውዝ፣ ሰሊጥ፣ ኑግ፣ ሱፍ፣ ተልባ)፣ 4ኛ. የእንስሣት ተዋፅዖ (የዶሮ፣ የከብት፣ የፍየል፣ የበግ ሥጋ እና ዓሣ፣ ዓይብ፣ እርጎ)፣ 5ኛ. አትክልትና ፍራፍሬ (እንደ ወጥ ወይም ሰላጣ የሚዘጋጁ አትክልቶች፣ ሙዝ፣ ብርቱካን፣ አቮካዶና ሌሎች ፍራፍሬዎች) እንዲሁም 6ኛ. ቅቤ እና ዘይት መሆናቸውን አብራርተዋል። ጤናማ ምግብ ደኅንነነቱ የተጠበቀ መሆን እንዳለበት ገልጸው፤ የኑሮ ሁኔታና ዐቅም በፈቀደ መጠን አመጋገብን ጤናማ በማድረግ ቀድሞ በበሽታ የመያዝ ዕድልን መቀነስ እንደሚቻል ባለሙያው መክረዋል።
በማዕድን ዘርፍ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች አስፈላጊው ድጋፍ ይደረጋል - ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኘ(ኢ/ር)
Nov 16, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ በማዕድን ዘርፍ ያለውን እምቅ ሀብት ወደ ብልፅግና ለመቀየር መንግስት በዘርፉ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የማዕድን ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኘ(ኢ/ር) ገለፁ። በማዕድን ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከህዳር 4 እስከ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው 4ኛው ዓለም አቀፍ የማዕድን እና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ(MINTEX Ethiopia 2025) በስኬት እንዲጠናነቅ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት የምስጋና እና የመዝጊያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ ወቅት የማዕድን ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኘ(ኢ/ር) እንዳሉት በማዕድን ዘርፍ ያለውን እምቅ ሀብት ወደ ብልፅግና ለመቀየር መንግስት በዘርፉ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነው። ባለፉት አመታት የማዕድን ዘርፉን ተግዳሮት ለመፍታት የሚያስችሉ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ነው የተናገሩት። ለማዕድን ኢንዱስትሪው በተሰጠው ትኩረት ምክንያት በማዕድን ሀብት ማስተዋወቅ እና በፕሮጀክት አስተዳደር ላይ ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑንም ገልጸዋል። ባለፉት ቀናት ሲካሄድ በቆየው ኤክስፖ ትምህርት የሚሰጡ ጥናቶች መቅረባቸውን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የማዕድን ዘርፉ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት የሚያሳልጥ በመሆኑ ያለንን እምቅ ሀብት ወደ ብልፅግና ለመቀየር በሚደረገው ጥረት ላይ መሳተፍ ለሚፈልጉ ኢንቨስተሮች ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን ብለዋል። ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፉ መሰማራት ከሚፈልጉ ኢንቨስተሮች ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላትም ነው የተናገሩት። በምስጋና እና መዝጊያ መርሃ ግብሩ ለኤክስፖው መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጥቷል። አራተኛውን ዓለም አቀፍ የማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ (MINTEX Ethiopia 2025) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ መከፈቱ ይታወቃል።
ኢንስቲቲዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Nov 16, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ ኢንስቲቲዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል ሲሉም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ጽሕፈት ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት በመለወጥ መሃል ከተማ ወደ ቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሕንፃ አዛውሯል ብለዋል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የግንባታ ለውጥ እና ዘመናዊ የመሥሪያ ሥፍራ ጥበብን በማሳየት ለሠራተኞቹ እጅግ ምቹ የሆነ ስፍራንም መፍጠር ችሏል ነው ያሉት። ተቋሙ በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሕይወታችንን በፍጥነት በመቅረጽ ውስጥ ያለውን ስፍራ በሚያንፀባርቅ እና ሀገራችንም በዚህ አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ውድድር በንቁነት መሳተፏን በሚያረጋግጥ መንገድ ከፍታ ላይ ደርሷል ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ሲሆን በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል ነው ያሉት። በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ መዐከል ደግሞ ይኽንን ከባቢ የበለጠ ያጠናክረዋል ብለዋል በመልዕክታቸው። ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል። እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቅመዋል ሲሉም አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያውያን ታላቁን የአፍሪካ ግድብ ያለምንም የውጭ እርዳታ እውን በማድረግ ታሪክ ሰርተዋል-ጋናዊው ዩቱበር ዎዴ ማያ
Nov 16, 2025 55
አዲስ አበባ፤ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን ታላቁን የአፍሪካ ግድብ ያለምንም የውጭ እርዳታ እውን በማድረግ ታሪክ ሰርተዋል ሲል ጋናዊው ዩቱበር ዎዴ ማያ ገለጸ። በማህበራዊ ትስስር ገጾች በተለይም በዪቱብ ስራዎቹ አለም ላይ በመዘዋወር የተለያዩ ፕሮግራሞችን በመስራት የሚታወቀው ጋናዊው ዎዴ ማያ፣ታላቁን የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በመጎብኘት ዘጋቢ ፊልም አሰናድቷል። በፕሮጀክቱ አጠቃላይ ስራ እጅግ መደመሙን የገለጸው ዎዴ ማያ፤ታላቁ የህዳሴ ግድብን ሰርቶ ለማጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን ያሳዩት አንድነት ለመላው አፍሪካ ትልቅ ትምህርት ነው ይላል። ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም የውጭ እርዳታ እንዴት ታላቁን የአፍሪካ ግድብ ገነቡ? የሚለው ጥያቄም አንድ ሀገር ያለውን ሀብት በአግባቡ ከተጠቀመ ታሪክ መስራት እንደሚችል ይህ ግድብ ማሳያ ነው ብሏል። በመሆኑም አፍሪካውያን ያለንን ሀብት ለሀገራዊ እድገት እና ብልጽግና በአግባቡ ከተጠቀምን ተራራ ማንቀሳቀስ እንችላለን በማለት አስረድቷል። ኢትዮጵያውያን የገነቡት ይህ ግድብ በአህጉሪቱ ግዙፍ እና በአፍሪካውያን ዘንድም እንደ ልህቀት የሚታይ ፕሮጀክት መሆኑን ነው የገለጸው። እንደ አንድ አፍሪካዊ ይህንን በማየቴ ኩራት ተሰምቶኛል የሚለው ዎዴ ማያ፤ታላቁ የህዳሴ ግድብ ሁሉም አፍሪካዊ ሊያየው የሚገባ ፓን አፍሪካዊ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጿል። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ አሻራውን ያሳረፈበት መሆኑን ገልጾ፥ አፍሪካዊያንም ከውጭ እርዳታ ሳንጠብቅ በትብብርና በጋራ ከሰራን አህጉራችንን ማበልጸግ እንችላለን ሲልም ተናግሯል። ዎዴ ማያ አክሎም፥ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ሁለተኛው ዓድዋ ነው ማለት ይቻላል ምክንያቱም በዓድዋ ጦርነት ወቅት ኢትዮጵያዊያን ተባብረው ጠላትን ድል እንዳደረጉት ሁሉ ይህ ፕሮጀክትም አፍሪካዊያን በምዕራባዊያን ላይ የነበራቸውን ጥገኝነት ያስቀረ እና በራስ አቅም የተሰራ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑንም ነው የገለጸው። ኢትዮጵያውያን በጽናት በመቆም ተባብረው ታላቁን የአፍሪካ ግድብ ያለምንም የውጭ እርዳታ እውን በማድረግ ታሪክ መስራት መቻላቸውን መስክሯል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት ያላትን ሚና አውስትራሊያ ትደግፋለች- አምባሳደር ፒተር ሃንተር
Nov 16, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት ውስጥ እየተወጣች ያለውን ትርጉም ያለው ሚና አውስትራሊያ እንደምትደግፍ አምባሳደር ፒተር ሃንተር (ዶ/ር) ገለጹ። አውስትራሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በአዳዲስ መስኮች ትብብር የመፍጠር ፍላጎት አላት ብለዋል። በኢትዮጵያ የአውስትራሊያ አምባሳደር ፒተር ሃንተር (ዶ/ር) የአፍሪካ ቀንድ ውስብስብ ፈተናዎች ያሉበት ቀጣና እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት እያደረገች ያለውን ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ እንደምትደግፍም አመልክተዋል። አምባሳደር ሃንተር አውስትራሊያ እና ኢትዮጵያ ያላቸው የሁለትዮሽ የትብብር አድማስ እየሰፋ እንደሚገኝ አንስተዋል። የህዝብ ለህዝብ ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ትምህርትን በማሳያነት ጠቅሰዋል። የአውስትራሊያ መንግስት ከኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር በቅርበት እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት። አምባሳደሩ ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለችውን የኢኮኖሚ ሪፎርሞች ያደነቁ ሲሆን ሪፎርሙ የባለሀብቶችን የራስ መተማመን መጨመሩንና አዳዲስ እድሎችን መፍጠሩን አብራርተዋል። አውስትራሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በቱሪዝም፣ ማዕድን እና ግብርና ዘርፍ ያላትን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። በተጨማሪም አምባሳደሩ ለአዲስ አበባ ለውጥ ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ይህም የኢትዮጵያን እድገት ምልክት ነው ብለዋል። ከዓለም አቀፍ ጉዳዮች ጋር በተገናኘም አውስትራሊያ የባለብዙወገን መድረክ ማሻሻያ እንዲደረግ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግና አፍሪካ በዓለም የወሳኔ ሰጪነት ውስጥ ያላት ሚና ማደግ እንደሚገባው አመልክተዋል። አውስትራሊያ ደህንነት እና ልማትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር እንደምትሻም አክለዋል
የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ ሰላምንና አብሮነትን በማስቀደም ለብልጽግና የምታደርጉትን ርብርብ ማስቀጠል አለባችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 15, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ ሰላምንና አብሮነትን በማስቀደም ለብልጽግና የምታደርጉትን ርብርብ ማስቀጠል አለባችሁ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በከሚሴ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ የወሎን የመሰለ የልብ ፍቅር ካለ ክፋት እና ጥላቻ መቼም እንደማያሸንፉ ገልጸዋል፡፡ የልብ ፍቅር ምን እንደሆነ ለሚያውቀው እና ፍቅርን በተግባር እየኖረ ላለው ለከሚሴ እና ለወሎ ሕዝብ መንገር አይጠበቅብንም ሲሉም ተናግረዋል። ከወሎ ሕዝብ የሚመነጭ ፍቅር እንኳን ለወሎ ለመላው ኢትዮጵያም የሚተርፍ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡ የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ እንደሚያውቀው ሰላም ከእውነተኛ ልብ ይመነጫል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዚህም ለሌላውም የሚተርፍ ፍቅር እንዳለው ጠቅስዋል፡፡ የከሚሴ ሕዝብ በፍቅር እና በጠንካራ ሠራተኛነቱ የሚታወቅ ህዝብ መሆኑንም ተናግረዋል። ፍቅር ከልብ እንደሚመነጨው ሁሉ ሰላምም ከውስጥ ይመነጫል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውስጡ ሰላም የሌለው ከውጪ ለመግዛት ቢሞክር እንደማይችል ገልጽዋል። በመሆኑም ሰላም ሁልግዜም ከውስጥ መጥፋት የሌለበትና ለሌሎችም የምታስተምሩት መሆን አለበት ብለዋል። ከዚህ በፊት በአንድነት አስቸጋር የነበሩ ግዚያትን አሳልፋችኋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከአሁን በኋላ ግን ቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ኑሮ እንዲኖር በጋራ እንሰራለን ነው ያሉት።
ሰራዊታችን በባንዳነት በተሰለፈው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን እያፀና ነው - ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ
Nov 15, 2025 97
ባሕርዳር፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፡- ሰራዊቱ የኢትዮዽያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ በመሆን በባንዳነት በተሰለፈው ፅንፈኛ ቡድን ላይ ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በዘላቂነት እያፀና መሆኑን የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ ገለጹ፡፡ ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ፤ በሰሜን ጎጃም እና በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች በግዳጅ ላይ የሚገኘውን ኮር የግዳጅ አፈጻጸም የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ከመስክ ምልከታቸውም በኋላ ከዞንና ከወረዳ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አመራሮች ጋር የተወያዩ ሲሆን በሰሜን አቸፈር ወረዳ ሊበን ከተማ በአንድ ክፍለ ጦር የስልጠና ማጠናቀቂያ ላይ በመገኘትም የስራ መመሪያና ስምሪት ሰጥተዋል። ሌተናል ጄኔራሉ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሰራዊቱ የኢትዮዽያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ በመሆን በባንዳነት የተሰለፈውን ፅንፈኛ ቡድን ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በዘላቂነት እያፀና ይገኛል ብለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች በመሽሎክሎክ ሕብረተሰቡን በማገትና በመዝረፍ ወንጀል የሚፈፅመውን ፅንፈኛ ቡድን ሰራዊቱ ከሕዝቡ ጋር በመተባበር ተከታትሎ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተው፤ ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመቀበል በክህደት በዜጎች ላይ ወንጀል ለመፈፀም የሚንቀሳቀሰውን ፅንፈኛ ቡድን በየደረጃው የሚገኘው አመራር፣ ሕዝቡና የፀጥታ ሃይሉ በትብብር ሕግ የማስከበር ስራውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። በኢትዮዽያ ሁሉም አካባቢዎች ሰላምን በማፅናትና የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማሳካት የኢትዮጵያን እድገትና ብልፅግና ማረጋገጥ የሁላችንም አደራ እና ሃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የሰላምና የጀግንነት ተምሳሌት የሆነው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለኢትዮዽያ ክብርና ሉአላዊነት መከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ በላቀ ዝግጁነት የሚገኝ መሆኑን ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ አረጋግጠዋል።
በክልሉ የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቷል - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Nov 15, 2025 72
ጋምቤላ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ውይይት አካሂደዋል። ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የክልሉ ህዝብ አንድነቱንና አብሮነቱን በማጠናከር መንግስት የጀመረውን የዘላቂ ሰላም ግንባታና የልማት ስራዎች ማገዝ ይጠበቅበታል። የክልሉ አመራርም የአስተሳሰብና የተግባር አንድነቱን በማጠናከር በክልሉ የታለሙ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶችን ዳር ለማድረስ ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በክልሉ የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ነው ያሉት። በክልሉ የሚፈለገውን ልማትና እድገት ማሳካት የሚቻላው ዘላቂ ሰላምን ማስፈን ሲቻል መሆኑን ጠቁመው የክልሉን ሰላም ለማደናቀፍ የሚሰሩ አካላትን በጋራ መታገል ይገባል ብለዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) በበኩላቸው ዘላቂ ሰላም በማስፈን የተጀመሩ የልማት እቅዶችን ለማሳካት ህዝብን አስተባብረን ልንሰራ ይገባል ነው ያሉት። በተለይም የክልሉን ሰላም ለማወክ የሚሰሩ አካላትን እኩይ ተግባር በመመከቱ ረገድ ሁሉም በጋራ ተባብሮ መስራት እንደለበት ገልጸዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ስራዎችን በማጎልበት መልካም እሴቶችን ማጠናከር ላይ ትኩረት አድረጎ መሰራት እንዳለበት ያመለከቱት ደግሞ የክልሉ መንግስት የዴሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሸኔ አስቲን ናቸው።
የድሬዳዋ ልማትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል - ከንቲባ ከድር ጁሃር
Nov 15, 2025 116
ድሬደዋ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የድሬዳዋ ልማትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። ጉባኤው በሁለት ቀናት ቆይታው በአገርና በድሬዳዋ ልማት፣ ሰላም እና ዘላቂ ዕድገት ላይ ወጣቱ ያለውን አበርክቶ እና ተጠቃሚነት ይገመግማል ተብሏል። በጉባኤ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንደተናገሩት ወጣቶች የድሬደዋን የብልጽግና ጉዞና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የላቀ ሚናቸውን እየተወጡ ናቸው። ወጣቶች በድሬዳዋ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ያላቸውን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማስቀጠልም አስተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። አገራዊ ለውጡ ወጣቶች በግልና በማህበር ታቅፈው በገጠርና በከተማ ልማት እንዲሳተፉ ማገዙን የገለጹት፤ ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽነር ካሊድ መሐመድ ናቸው። ወጣቶች በበጋ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በመሳተፍ የአረጋውያንን ቤቶች በመገንባት፣ ደም በመለገስ፣ ማዕድ በማጋራት፣ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ሰላምን በማረጋገጥ ላይ በንቃት በመሳተፍ ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆናቸውን አንስተዋል። እነዚህን ስራዎች ከማጠናከር ጎን ለጎን በሁሉም ዘርፍ ያላቸውን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ጉባኤው መሠረታዊ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ ተናግረዋል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወጣት ሃሚድ አብደላ በበኩሉ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ ለወጣቶች የተሰጠው ትኩረት የወጣቱን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን አንስቷል። እነዚህን እንቅስቃሴዎች በማጠናከር የድሬዳዋን ዘላቂ ሰላምና የልማት ጉዞ ከዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል። ለሁለት ቀናት የሚካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ በአገራዊ መሠረታዊ አቅጣጫዎች ላይ በመወያየት የተሻለ ስራ ለማከናወን የሚያስችል ሁኔታ የሚፈጠር መሆኑን በማረጋገጥ ።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ በሂደቱ የድርሻችንን እንወጣለን - የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Nov 15, 2025 85
አዳማ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለምላሹ በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ ማንሳታቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የተለያዩ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ህልውና ጉዳይ እና የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ነው ብለዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ የመንግስትን ጠንካራ አቋም ያደነቁት አመራሮቹ ለስኬቱ ሁላችንም አደራ እና ሃላፊነት አለብን ሲሉም ተናግረዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለምላሹ በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል። ከፓርቲዎቹ አመራሮች መካከል የቤንሻንጉል ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ በሁሉም መመዘኛዎች ትክክልና ምላሽ ማግኘት ያለበት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ፓርቲያቸው የመንግስትን አቋም በመደገፍ ለተግባራዊነቱ የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። የትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ለብሔራዊ ጥቅም መከበር በጋራ መቆም እንዳለበት እናምናለን ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ጥያቄው ምላሽ እንዲያገኝ እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድ ልብ እንሰራለን ብለዋል። ፓርቲው በቀጣይም ለሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች ስለ ባሕር በር አስፈላጊነትና ብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ ግልፅ ግንዛቤና አረዳድ እንዲኖረው የሚጠበቅብትን ይወጣል ነው ያሉት። የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አለማየሁ ሻሮ በበኩላቸው፤ የባሕር በር ጥያቄ በግልፅ መነሳቱ ትክክለኛ እና ወቅቱን የጠበቀ በመሆኑ የሚደገፍ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ለመልማት፣ ለማደግ፣ የወጪና ገቢ ምርቶችን ለማሳለጥ የግድ የባሕር በር ያስፈልጋታል ያሉት አቶ አለማየሁ፤ ጉዳዩ ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ የሚጠበቅባቸው እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። መንግስት ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ በሆነ አካሄድ የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ እያደረገ ያለው ጥረት በመደገፍ ሁላችንም በጋራ በመቆም መረባረብ አለብን ነው ያሉት። የባሕር በር ጉዳይ ትውልድና ሀገርን የማስቀጠል የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለስኬታማነቱ የሚጠበቅብንን እንወጣለን ያሉት ደግሞ የኩሽ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ፓርቲ ፕሬዘዳንት ማንአይቶት በየነ ናቸው። ፓርቲያቸው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄው ትክክለኛና ፍትሃዊ መሆኑን አመልክተው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በዚህ ወሳኝ ጉዳይ በጋራ በመቆም መረባረብ አለብን ብለዋል።
“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት አገኘ
Nov 15, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ሰጥቷል። ለትግራይ ክልል አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ ለማቅረብ ወጣቶች የፖለቲካ ፓርቲ በመመስረት ሕጋዊ ማረጋገጫ እንዲሰጣቸው ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ ማቅረባቸው ተመላክቷል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጁ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለ“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ኅዳር 05 ቀን 2018 ዓ.ም. መስጠቱን አስታውቋል።
በጋምቤላ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል
Nov 15, 2025 69
ጋምቤላ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ በተለያዩ ሁነቶች ለማክበር ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ መሰረት ማቲዎስ ገለጹ። አፈ-ጉባዔዋ አከባበሩን አስመልክተው እንዳስታወቁት፤ 20ኛው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በክልል ደረጃ በአኝዋሃ ዞን ዲማ ወረዳ አስተናጋጅነት በድምቀት ይከበራል። ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ለማክበር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። በዓሉ በክልሉ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች በባህላዊ እሴቶቻቸው የሚያሳዩበትና ይህም የቱሪዝም ልማቱን ለማጎልበት በሚደረገው ጥረት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በዓሉ በክልሉ በሚገኙ የአስተዳደር እርከኖችና አደረጃጀቶች በፌዴራሊዝም ሥርዓትና በህገ መንግስት አስተምሮን ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረኮች እየተካሄዱ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም በትምህርት ቤቶች በጥያቄና መልስ እና በስፖርታዊ ውድድሮች እንዲሁም በሌሎች ሁነቶች በዓሉ እንደሚከበርም አንስተዋል። አካባበሩ በክልል ደረጃ እስከ ህዳር 20/2018ዓ.ም በማጠናቀቅ በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሚከበረው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ላይ ለመታደም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ለኢዜአ ጨምረው ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት ያላትን ሚና አውስትራሊያ ትደግፋለች- አምባሳደር ፒተር ሃንተር
Nov 16, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት ውስጥ እየተወጣች ያለውን ትርጉም ያለው ሚና አውስትራሊያ እንደምትደግፍ አምባሳደር ፒተር ሃንተር (ዶ/ር) ገለጹ። አውስትራሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በአዳዲስ መስኮች ትብብር የመፍጠር ፍላጎት አላት ብለዋል። በኢትዮጵያ የአውስትራሊያ አምባሳደር ፒተር ሃንተር (ዶ/ር) የአፍሪካ ቀንድ ውስብስብ ፈተናዎች ያሉበት ቀጣና እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት እያደረገች ያለውን ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ እንደምትደግፍም አመልክተዋል። አምባሳደር ሃንተር አውስትራሊያ እና ኢትዮጵያ ያላቸው የሁለትዮሽ የትብብር አድማስ እየሰፋ እንደሚገኝ አንስተዋል። የህዝብ ለህዝብ ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ትምህርትን በማሳያነት ጠቅሰዋል። የአውስትራሊያ መንግስት ከኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር በቅርበት እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት። አምባሳደሩ ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለችውን የኢኮኖሚ ሪፎርሞች ያደነቁ ሲሆን ሪፎርሙ የባለሀብቶችን የራስ መተማመን መጨመሩንና አዳዲስ እድሎችን መፍጠሩን አብራርተዋል። አውስትራሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በቱሪዝም፣ ማዕድን እና ግብርና ዘርፍ ያላትን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። በተጨማሪም አምባሳደሩ ለአዲስ አበባ ለውጥ ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ይህም የኢትዮጵያን እድገት ምልክት ነው ብለዋል። ከዓለም አቀፍ ጉዳዮች ጋር በተገናኘም አውስትራሊያ የባለብዙወገን መድረክ ማሻሻያ እንዲደረግ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግና አፍሪካ በዓለም የወሳኔ ሰጪነት ውስጥ ያላት ሚና ማደግ እንደሚገባው አመልክተዋል። አውስትራሊያ ደህንነት እና ልማትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር እንደምትሻም አክለዋል
የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ ሰላምንና አብሮነትን በማስቀደም ለብልጽግና የምታደርጉትን ርብርብ ማስቀጠል አለባችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 15, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ ሰላምንና አብሮነትን በማስቀደም ለብልጽግና የምታደርጉትን ርብርብ ማስቀጠል አለባችሁ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በከሚሴ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ የወሎን የመሰለ የልብ ፍቅር ካለ ክፋት እና ጥላቻ መቼም እንደማያሸንፉ ገልጸዋል፡፡ የልብ ፍቅር ምን እንደሆነ ለሚያውቀው እና ፍቅርን በተግባር እየኖረ ላለው ለከሚሴ እና ለወሎ ሕዝብ መንገር አይጠበቅብንም ሲሉም ተናግረዋል። ከወሎ ሕዝብ የሚመነጭ ፍቅር እንኳን ለወሎ ለመላው ኢትዮጵያም የሚተርፍ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡ የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ እንደሚያውቀው ሰላም ከእውነተኛ ልብ ይመነጫል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዚህም ለሌላውም የሚተርፍ ፍቅር እንዳለው ጠቅስዋል፡፡ የከሚሴ ሕዝብ በፍቅር እና በጠንካራ ሠራተኛነቱ የሚታወቅ ህዝብ መሆኑንም ተናግረዋል። ፍቅር ከልብ እንደሚመነጨው ሁሉ ሰላምም ከውስጥ ይመነጫል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውስጡ ሰላም የሌለው ከውጪ ለመግዛት ቢሞክር እንደማይችል ገልጽዋል። በመሆኑም ሰላም ሁልግዜም ከውስጥ መጥፋት የሌለበትና ለሌሎችም የምታስተምሩት መሆን አለበት ብለዋል። ከዚህ በፊት በአንድነት አስቸጋር የነበሩ ግዚያትን አሳልፋችኋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከአሁን በኋላ ግን ቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ኑሮ እንዲኖር በጋራ እንሰራለን ነው ያሉት።
ሰራዊታችን በባንዳነት በተሰለፈው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን እያፀና ነው - ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ
Nov 15, 2025 97
ባሕርዳር፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፡- ሰራዊቱ የኢትዮዽያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ በመሆን በባንዳነት በተሰለፈው ፅንፈኛ ቡድን ላይ ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በዘላቂነት እያፀና መሆኑን የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ ገለጹ፡፡ ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ፤ በሰሜን ጎጃም እና በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች በግዳጅ ላይ የሚገኘውን ኮር የግዳጅ አፈጻጸም የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ከመስክ ምልከታቸውም በኋላ ከዞንና ከወረዳ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አመራሮች ጋር የተወያዩ ሲሆን በሰሜን አቸፈር ወረዳ ሊበን ከተማ በአንድ ክፍለ ጦር የስልጠና ማጠናቀቂያ ላይ በመገኘትም የስራ መመሪያና ስምሪት ሰጥተዋል። ሌተናል ጄኔራሉ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሰራዊቱ የኢትዮዽያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ በመሆን በባንዳነት የተሰለፈውን ፅንፈኛ ቡድን ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በዘላቂነት እያፀና ይገኛል ብለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች በመሽሎክሎክ ሕብረተሰቡን በማገትና በመዝረፍ ወንጀል የሚፈፅመውን ፅንፈኛ ቡድን ሰራዊቱ ከሕዝቡ ጋር በመተባበር ተከታትሎ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተው፤ ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመቀበል በክህደት በዜጎች ላይ ወንጀል ለመፈፀም የሚንቀሳቀሰውን ፅንፈኛ ቡድን በየደረጃው የሚገኘው አመራር፣ ሕዝቡና የፀጥታ ሃይሉ በትብብር ሕግ የማስከበር ስራውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። በኢትዮዽያ ሁሉም አካባቢዎች ሰላምን በማፅናትና የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማሳካት የኢትዮጵያን እድገትና ብልፅግና ማረጋገጥ የሁላችንም አደራ እና ሃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የሰላምና የጀግንነት ተምሳሌት የሆነው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለኢትዮዽያ ክብርና ሉአላዊነት መከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ በላቀ ዝግጁነት የሚገኝ መሆኑን ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ አረጋግጠዋል።
በክልሉ የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቷል - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Nov 15, 2025 72
ጋምቤላ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ውይይት አካሂደዋል። ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የክልሉ ህዝብ አንድነቱንና አብሮነቱን በማጠናከር መንግስት የጀመረውን የዘላቂ ሰላም ግንባታና የልማት ስራዎች ማገዝ ይጠበቅበታል። የክልሉ አመራርም የአስተሳሰብና የተግባር አንድነቱን በማጠናከር በክልሉ የታለሙ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶችን ዳር ለማድረስ ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በክልሉ የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ነው ያሉት። በክልሉ የሚፈለገውን ልማትና እድገት ማሳካት የሚቻላው ዘላቂ ሰላምን ማስፈን ሲቻል መሆኑን ጠቁመው የክልሉን ሰላም ለማደናቀፍ የሚሰሩ አካላትን በጋራ መታገል ይገባል ብለዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) በበኩላቸው ዘላቂ ሰላም በማስፈን የተጀመሩ የልማት እቅዶችን ለማሳካት ህዝብን አስተባብረን ልንሰራ ይገባል ነው ያሉት። በተለይም የክልሉን ሰላም ለማወክ የሚሰሩ አካላትን እኩይ ተግባር በመመከቱ ረገድ ሁሉም በጋራ ተባብሮ መስራት እንደለበት ገልጸዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ስራዎችን በማጎልበት መልካም እሴቶችን ማጠናከር ላይ ትኩረት አድረጎ መሰራት እንዳለበት ያመለከቱት ደግሞ የክልሉ መንግስት የዴሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሸኔ አስቲን ናቸው።
የድሬዳዋ ልማትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል - ከንቲባ ከድር ጁሃር
Nov 15, 2025 116
ድሬደዋ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የድሬዳዋ ልማትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። ጉባኤው በሁለት ቀናት ቆይታው በአገርና በድሬዳዋ ልማት፣ ሰላም እና ዘላቂ ዕድገት ላይ ወጣቱ ያለውን አበርክቶ እና ተጠቃሚነት ይገመግማል ተብሏል። በጉባኤ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንደተናገሩት ወጣቶች የድሬደዋን የብልጽግና ጉዞና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የላቀ ሚናቸውን እየተወጡ ናቸው። ወጣቶች በድሬዳዋ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ያላቸውን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማስቀጠልም አስተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። አገራዊ ለውጡ ወጣቶች በግልና በማህበር ታቅፈው በገጠርና በከተማ ልማት እንዲሳተፉ ማገዙን የገለጹት፤ ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽነር ካሊድ መሐመድ ናቸው። ወጣቶች በበጋ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በመሳተፍ የአረጋውያንን ቤቶች በመገንባት፣ ደም በመለገስ፣ ማዕድ በማጋራት፣ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ሰላምን በማረጋገጥ ላይ በንቃት በመሳተፍ ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆናቸውን አንስተዋል። እነዚህን ስራዎች ከማጠናከር ጎን ለጎን በሁሉም ዘርፍ ያላቸውን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ጉባኤው መሠረታዊ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ ተናግረዋል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወጣት ሃሚድ አብደላ በበኩሉ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ ለወጣቶች የተሰጠው ትኩረት የወጣቱን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን አንስቷል። እነዚህን እንቅስቃሴዎች በማጠናከር የድሬዳዋን ዘላቂ ሰላምና የልማት ጉዞ ከዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል። ለሁለት ቀናት የሚካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ በአገራዊ መሠረታዊ አቅጣጫዎች ላይ በመወያየት የተሻለ ስራ ለማከናወን የሚያስችል ሁኔታ የሚፈጠር መሆኑን በማረጋገጥ ።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ በሂደቱ የድርሻችንን እንወጣለን - የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Nov 15, 2025 85
አዳማ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለምላሹ በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ ማንሳታቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የተለያዩ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ህልውና ጉዳይ እና የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ነው ብለዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ የመንግስትን ጠንካራ አቋም ያደነቁት አመራሮቹ ለስኬቱ ሁላችንም አደራ እና ሃላፊነት አለብን ሲሉም ተናግረዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለምላሹ በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል። ከፓርቲዎቹ አመራሮች መካከል የቤንሻንጉል ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ በሁሉም መመዘኛዎች ትክክልና ምላሽ ማግኘት ያለበት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ፓርቲያቸው የመንግስትን አቋም በመደገፍ ለተግባራዊነቱ የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። የትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ለብሔራዊ ጥቅም መከበር በጋራ መቆም እንዳለበት እናምናለን ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ጥያቄው ምላሽ እንዲያገኝ እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድ ልብ እንሰራለን ብለዋል። ፓርቲው በቀጣይም ለሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች ስለ ባሕር በር አስፈላጊነትና ብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ ግልፅ ግንዛቤና አረዳድ እንዲኖረው የሚጠበቅብትን ይወጣል ነው ያሉት። የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አለማየሁ ሻሮ በበኩላቸው፤ የባሕር በር ጥያቄ በግልፅ መነሳቱ ትክክለኛ እና ወቅቱን የጠበቀ በመሆኑ የሚደገፍ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ለመልማት፣ ለማደግ፣ የወጪና ገቢ ምርቶችን ለማሳለጥ የግድ የባሕር በር ያስፈልጋታል ያሉት አቶ አለማየሁ፤ ጉዳዩ ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ የሚጠበቅባቸው እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። መንግስት ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ በሆነ አካሄድ የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ እያደረገ ያለው ጥረት በመደገፍ ሁላችንም በጋራ በመቆም መረባረብ አለብን ነው ያሉት። የባሕር በር ጉዳይ ትውልድና ሀገርን የማስቀጠል የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለስኬታማነቱ የሚጠበቅብንን እንወጣለን ያሉት ደግሞ የኩሽ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ፓርቲ ፕሬዘዳንት ማንአይቶት በየነ ናቸው። ፓርቲያቸው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄው ትክክለኛና ፍትሃዊ መሆኑን አመልክተው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በዚህ ወሳኝ ጉዳይ በጋራ በመቆም መረባረብ አለብን ብለዋል።
“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት አገኘ
Nov 15, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ሰጥቷል። ለትግራይ ክልል አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ ለማቅረብ ወጣቶች የፖለቲካ ፓርቲ በመመስረት ሕጋዊ ማረጋገጫ እንዲሰጣቸው ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ ማቅረባቸው ተመላክቷል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጁ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለ“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ኅዳር 05 ቀን 2018 ዓ.ም. መስጠቱን አስታውቋል።
በጋምቤላ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል
Nov 15, 2025 69
ጋምቤላ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ በተለያዩ ሁነቶች ለማክበር ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ መሰረት ማቲዎስ ገለጹ። አፈ-ጉባዔዋ አከባበሩን አስመልክተው እንዳስታወቁት፤ 20ኛው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በክልል ደረጃ በአኝዋሃ ዞን ዲማ ወረዳ አስተናጋጅነት በድምቀት ይከበራል። ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ለማክበር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። በዓሉ በክልሉ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች በባህላዊ እሴቶቻቸው የሚያሳዩበትና ይህም የቱሪዝም ልማቱን ለማጎልበት በሚደረገው ጥረት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በዓሉ በክልሉ በሚገኙ የአስተዳደር እርከኖችና አደረጃጀቶች በፌዴራሊዝም ሥርዓትና በህገ መንግስት አስተምሮን ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረኮች እየተካሄዱ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም በትምህርት ቤቶች በጥያቄና መልስ እና በስፖርታዊ ውድድሮች እንዲሁም በሌሎች ሁነቶች በዓሉ እንደሚከበርም አንስተዋል። አካባበሩ በክልል ደረጃ እስከ ህዳር 20/2018ዓ.ም በማጠናቀቅ በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሚከበረው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ላይ ለመታደም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ለኢዜአ ጨምረው ገልጸዋል።
ማህበራዊ
ለብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ወደ ክልሉ የሚመጡ እንግዶች የተለያዩ መስኅቦችን ይጎበኛሉ
Nov 17, 2025 19
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡- ለ20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን አከባበር ወደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሚመጡ እንግዶች የቱሪዝም መስኅቦችን ለማስጎብኘት ዝግጅት ተደርጓል። ቀኑ በክልሉ መከበሩ ተፈሯዊ፤ ታሪካዊና ባህላዊ የቱሪዝም መስኅቦች ለማስተዋወቅ እንደሚጠቅም የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትልና የቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ መሐመድኑሪ ሳልያ ተናግረዋል። በዚህም መሠረት እንግዶች ሲመጡ በቀላሉ እንዲጎበኟቸው ዋና ዋና የቱሪዝም መስኅቦች ተለይተው በቂ ዝግጅት መደረጉን ለኢዜአ አረጋግጠዋል። የተለዩት መዳረሻዎችም፤ ጥያ ዓለም አቀፍ መካነ ቅርስ፣ ምድረ ከብድ አቦ ገዳም፣ የስልጤ ሙዚየም፣ ሀረ ሸይጣን ሐይቅ፣ አርቶ ፍል ውኃ፣ ሴራ ፌስቲቫል፣ መጨፈራ ሐይቅ፣ ወገና የከብቶች ቆጠራ ሥርዓት፣ ሃምበርቾ 777 ኢኮ ቱሪዝም እና ሶዲቾ ዋሻ መሆናቸውን ገልጸዋል። እንዲሁም አጆራ ፏፏቴ፣ ጀፎር፣ ጊቤ ሸለቆ ብሔራዊ ፓርክ፣ ብርብርሳ ፏፏቴ፣ ጥቅምት 17 ባህላዊ የመድኃት ለቀማ የሚከናወንበት ስፍራ (ሳሞ ኤታ)፣ኦሞ ሰው ሠራሸ ሐይቅ፣ መሪሾ ፌስቲቫል፣ ዘቢሞላ ሀድራ፣ ደቀንሽ ሞላ ፏፏቴ፣ ራጋ ማጋ የግጭት አፈታት ሥርዓት እና ፋቃ ከንፈልቻ ዋሻ በእንግዶች እንዲጎበኙ የተለዩ መስኅቦች መሆናቸውን ተናግረዋል። በተጨማሪም የባህል ምግቦችና አለባበስን እንግዶች በሚያልፉበትና በሚያርፉበት ለማስተዋወቅ ትኩረት መሰጠቱን አስታውቀዋል። ሆቴሎችና የእንግዳ ማረፊያዎችን ጨምሮ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በክልሉ የእንግዳ ተቀባይነት ባህል እንግዶችን ለመቀበል መዘጋጀታቸውን አቶ መሐመድኑሪ አረጋግጠዋል።
ጤናማ አመጋገብ ሲባል ምን ማለት ነው?
Nov 17, 2025 46
በፈረንጆቹ 2024 የዓለም እርሻና ምግብ ድርጅት እና የዓለም ጤና ድርጅት ባወጡት መመሪያ መሠረት ጤናማ ምግብ አራት መሠረታዊ መርሆዎችን ይይዛል። እነሱም፤ በቂ መሆን፣ ሚዛንን መጠበቅ፣ ልከኝነት እና የተሰባጠረ መሆናቸውን የሥርዓተ-ምግብ፣ የአካባቢ ጤናና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ተመራማሪ ዳዊት ዓለማየሁ ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህም መሠረት፡- በቂ መሆን፦ ሁሉንም አስፈላጊ ንጥረ ነገሮችና እነሱን የያዙ የምግብ መደቦች በበቂ መጠን እንዲሁም ከፍላጎት በላይ ሳይሆን ማቅረብ ማለት ነው። በዚህም የአመጋገብ ፍላጎቶችን ከዕድሜ፣ ጾታ፣ የእንቅስቃሴ ደረጃ እና የፊዚዮሎጂ ሁኔታ ጋር ማመጣጠን አስፈላጊ ስለመሆኑ አስረድተዋል። ሚዛንን መጠበቅ፡- ማክሮኒዩትሬንቶች (ፕሮቲን፣ ስብና ካርቦሃይድሬት) እድገት፣ ጉልበትና አጠቃላይ ጤናን በሚደግፍ መጠን መወሰድ አለባቸው ብለዋል። ልከኝነት፡- ከጤና አደጋዎች ጋር የተገናኙ ንጥረ ነገሮች እንደ ስኳር፣ ሶዲየም (ጨው)፣ የሳቹሬትድ ፋት (ጠጣር ስብ) እና ትራንስ ፋት (ተፈጥሯዊ ባሕርይው በፋብሪካ የተቀየረ ስብ) በተጠበቀ ገደብ ውስጥ መሆን አለበት ማለት ነው። ይህም ለህመም ተጋላጭነትን ለመቀነስ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስብጥር፡- የተለያዩ የምግብ ዓይነቶችን በተመጣጠነ ሁኔታ ማካተት በቂ ንጥረ ነገሮችን ለማግኘት ከማስቻሉ በላይ የምግብ እጥረትን ለመከላከል ይረዳል ብለዋል። የተሰባጠረ አመጋገብ ማለት በአንድ ገበታ በአንድ ጊዜ ቢያንስ አራት የምግብ ምድብ እንዲሁም በቀን ስድስት የተለያየ የምግብ ምድብ የያዘ ማለት ነው። የኢትዮጵያ ምግብን-መሰረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ ስድስት የምግብ መደቦች መያዙን አብራርተዋል። በዚህም መሠረት፡- 1ኛ. እህልና ሥራሥር (እንጀራ፣ ዳቦ፣ ቆጮ እና ቆሎ)፣ 2ኛ. ጥራጥሬ (አተር፣ ምስር፣ ሽምብራ እና ባቄላ)፣ 3ኛ. ለውዝ እና የቅባት እህል (ለውዝ፣ ሰሊጥ፣ ኑግ፣ ሱፍ፣ ተልባ)፣ 4ኛ. የእንስሣት ተዋፅዖ (የዶሮ፣ የከብት፣ የፍየል፣ የበግ ሥጋ እና ዓሣ፣ ዓይብ፣ እርጎ)፣ 5ኛ. አትክልትና ፍራፍሬ (እንደ ወጥ ወይም ሰላጣ የሚዘጋጁ አትክልቶች፣ ሙዝ፣ ብርቱካን፣ አቮካዶና ሌሎች ፍራፍሬዎች) እንዲሁም 6ኛ. ቅቤ እና ዘይት መሆናቸውን አብራርተዋል። ጤናማ ምግብ ደኅንነነቱ የተጠበቀ መሆን እንዳለበት ገልጸው፤ የኑሮ ሁኔታና ዐቅም በፈቀደ መጠን አመጋገብን ጤናማ በማድረግ ቀድሞ በበሽታ የመያዝ ዕድልን መቀነስ እንደሚቻል ባለሙያው መክረዋል።
ኮሌጁ ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅነት ማደጉ ኃላፊነቱን የበለጠ ለመወጣት ያስችለዋል
Nov 16, 2025 55
ደብር ማርቆስ ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሌጅ ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅነት ማደጉ በጥናትና ምርምር ታግዞ የተጣለበትን የህዝብና የመንግስት ሀላፊነት የበለጠ ለመወጣት አቅም የሚፈጥርለት መሆኑ ተመለከተ። ኮሌጁ ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅነት እንዲያድግ አስተዋጽኦ ላደረጉና በተልዕኮ አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የኮሌጁ አመራሮችና አባላት ዛሬ የማዕረግ እድገትና እውቅና ተሰጥቷል። የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ፕሬዚዳንት ምክትል ኮሚኒሽነር አበበ ደለለ በወቅቱ እንደገለጹት፡ ኮሌጁ ከተቋቋመ ከ1985 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የፖሊስ አመራሮችና አባላትን በእውቅትና በክህሎት በማነጽ አፍርቷል። በዚህም የፖሊስ አመራሮችና አባላትን በአካል ብቃት፣ በስነ ምግባር፣ በእውቀትና በስነ ልቦና በማነጽ በክልሉ ሰላምን ለማስፈንና ወንጀልን ለመከላከል አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ኮሌጁ ከሐምሌ ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅነት ማደጉን ጠቁመው፣ ለዚህ ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉና በተልዕኮ አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የኮሌጁ አመራሮችና አባላት የማዕረግ እድገትና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል ብለዋል። ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ማደጉ በጥናትና ምርምር ላይ በማተኮር መንግስትና ህዝብ የጣሉበትን ሃላፊነት በተሻለ ለመወጣት ተነሳሽነትን ፈጥሯል ብለዋል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በበኩላቸው፤ ኮሌጁ የሰለጠነ የፖሊስ ሃይል በማፍራት ወንጀልን ለመከላከል በሚሰራው ሥራ ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው። ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅነት ማደጉ አሰራሩን በማዘመን የወንጀል መከላከል አቅሙን እንደሚያሳድገው ተናግረዋል። ኮሌጁ ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅነት ማደጉ አሰራሩን በማሳደግ በቴክኖሎጂና ምርምር ላይ አተኩሮ እንዲሰራ ያስችለዋል ያሉት ደግሞ የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ ናቸው። የማዕረግ እድገት ካገኙት መካከል ኮማንደር ታደለ ፈንቴ እንዳሉት የማዕረግ እድገቱ በቀጣይ በህብረተሰቡ ተሰትፎ ውጤታማ ሥራ ለመስራት የሚያነሳሳ ነው ብለዋል።
የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ የሁሉም አካል ርብርብ አስፈላጊ ነው
Nov 16, 2025 92
አዲስ አበባ፤ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ እና የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሁሉም አካል ርብርብ አስፈላጊ መሆኑን ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። የአፍሪካ የመንገድ ደህንነት ቀን ዛሬ ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አድዋ ድል መታሰቢያ እየተከበረ ይገኛል። የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ እና የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሁሉም አካላት ርብርብ አስፈላጊ ነው። በአፍሪካ በየዓመቱ የሚደርሰው የትራፊክ አደጋ አሳሳቢ መሆኑን ገልፀው ኢትዮጵያ የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው ብለዋል። ለአብነትም በኢትዮጵያ በሚገኙ የተለያዩ ከተሞች እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የመንገድ ደህንነት እንዲጠበቅ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህም ለእግረኞች፣ለብስክሌት እንዲሁም ለተሽከርካሪ ምቹ የሆኑ መንገዶች እየተገነቡ መሆኑን ጠቅሰው ይህም የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ጠቁመዋል። በአገሪቱ የመንገድ ደህንነትን የሚያስጠብቁ የህግ ማዕቀፎች መውጣታቸውን አስታውሰው ለትራፊክ አደጋ መንስኤ የሆኑ ችግሮችን በመለየት መፍትሔ ለመስጠት የተጀመሩ ስራዎች ውጤት እያስገኙ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ መተቦጌ በበኩላቸው እንደገለጹት በአፍሪካ የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው ። ኢትዮጵያ የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ የጀመረችው ጥረት የሚበረታታ እና ለሌሎች አገራት ምሳሌ መሆን የሚችል ነው ብለዋል ። በአፍሪካ የመንገድ ደህንነትንና ዘላቂ የትራንስፖርት እንቅስቃሴን ለማረጋገጥ የበለጠ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። በአፍሪካ ከፍተኛ የትራፊክ አደጋ እንደሚከሰት ጠቁመው ኮሚሽኑ አደጋውን ለመቀነስ የሚያስችሉ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በመንገድ ደህንነት ቀን የትራፊክ አደጋ ተጎጂዎች የሚታወሱ መሆኑን በመጠቆም እ.አ.አ በ2030 በአህጉሪቱ በትራፊክ አደጋ የሚደርሰውን ሞት በ50 በመቶ ለመቀነስ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ጀማል አባሶ በበኩላቸው እንደገለጹት የትራፊክ አደጋ በአገር ሰብዓዊ ሃብትና ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ነው። ችግሩን ለመፍታት የሁሉም ርብርብ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ህግ ለማስከበር የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል። በአገሪቱ ያለው የተሽከርካሪ ቁጥር አነስተኛ ቢሆንም የሚደርሰው አደጋ ግን ከፍተኛ ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚው ችግሩን ለመፍታት በቀጣይ ጠንካራ ስራ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በአገሪቱ በየደረጃው የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ 2012 ባሳለፈው ውሳኔ ቀኑ በየዓመቱ የሚከበር ሲሆን እለቱ ከዓለም የትራፊክ አደጋ ተጎጂዎች መታሰቢያ ቀን ጋር እንዲተሳሰር መደረጉ ተገልጿል።
ኢኮኖሚ
በማዕድን ዘርፍ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች አስፈላጊው ድጋፍ ይደረጋል - ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኘ(ኢ/ር)
Nov 16, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ በማዕድን ዘርፍ ያለውን እምቅ ሀብት ወደ ብልፅግና ለመቀየር መንግስት በዘርፉ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የማዕድን ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኘ(ኢ/ር) ገለፁ። በማዕድን ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከህዳር 4 እስከ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው 4ኛው ዓለም አቀፍ የማዕድን እና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ(MINTEX Ethiopia 2025) በስኬት እንዲጠናነቅ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት የምስጋና እና የመዝጊያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ ወቅት የማዕድን ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኘ(ኢ/ር) እንዳሉት በማዕድን ዘርፍ ያለውን እምቅ ሀብት ወደ ብልፅግና ለመቀየር መንግስት በዘርፉ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነው። ባለፉት አመታት የማዕድን ዘርፉን ተግዳሮት ለመፍታት የሚያስችሉ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ነው የተናገሩት። ለማዕድን ኢንዱስትሪው በተሰጠው ትኩረት ምክንያት በማዕድን ሀብት ማስተዋወቅ እና በፕሮጀክት አስተዳደር ላይ ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑንም ገልጸዋል። ባለፉት ቀናት ሲካሄድ በቆየው ኤክስፖ ትምህርት የሚሰጡ ጥናቶች መቅረባቸውን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የማዕድን ዘርፉ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት የሚያሳልጥ በመሆኑ ያለንን እምቅ ሀብት ወደ ብልፅግና ለመቀየር በሚደረገው ጥረት ላይ መሳተፍ ለሚፈልጉ ኢንቨስተሮች ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን ብለዋል። ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፉ መሰማራት ከሚፈልጉ ኢንቨስተሮች ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላትም ነው የተናገሩት። በምስጋና እና መዝጊያ መርሃ ግብሩ ለኤክስፖው መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጥቷል። አራተኛውን ዓለም አቀፍ የማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ (MINTEX Ethiopia 2025) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ መከፈቱ ይታወቃል።
ኢትዮጵያውያን ታላቁን የአፍሪካ ግድብ ያለምንም የውጭ እርዳታ እውን በማድረግ ታሪክ ሰርተዋል-ጋናዊው ዩቱበር ዎዴ ማያ
Nov 16, 2025 55
አዲስ አበባ፤ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን ታላቁን የአፍሪካ ግድብ ያለምንም የውጭ እርዳታ እውን በማድረግ ታሪክ ሰርተዋል ሲል ጋናዊው ዩቱበር ዎዴ ማያ ገለጸ። በማህበራዊ ትስስር ገጾች በተለይም በዪቱብ ስራዎቹ አለም ላይ በመዘዋወር የተለያዩ ፕሮግራሞችን በመስራት የሚታወቀው ጋናዊው ዎዴ ማያ፣ታላቁን የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በመጎብኘት ዘጋቢ ፊልም አሰናድቷል። በፕሮጀክቱ አጠቃላይ ስራ እጅግ መደመሙን የገለጸው ዎዴ ማያ፤ታላቁ የህዳሴ ግድብን ሰርቶ ለማጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን ያሳዩት አንድነት ለመላው አፍሪካ ትልቅ ትምህርት ነው ይላል። ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም የውጭ እርዳታ እንዴት ታላቁን የአፍሪካ ግድብ ገነቡ? የሚለው ጥያቄም አንድ ሀገር ያለውን ሀብት በአግባቡ ከተጠቀመ ታሪክ መስራት እንደሚችል ይህ ግድብ ማሳያ ነው ብሏል። በመሆኑም አፍሪካውያን ያለንን ሀብት ለሀገራዊ እድገት እና ብልጽግና በአግባቡ ከተጠቀምን ተራራ ማንቀሳቀስ እንችላለን በማለት አስረድቷል። ኢትዮጵያውያን የገነቡት ይህ ግድብ በአህጉሪቱ ግዙፍ እና በአፍሪካውያን ዘንድም እንደ ልህቀት የሚታይ ፕሮጀክት መሆኑን ነው የገለጸው። እንደ አንድ አፍሪካዊ ይህንን በማየቴ ኩራት ተሰምቶኛል የሚለው ዎዴ ማያ፤ታላቁ የህዳሴ ግድብ ሁሉም አፍሪካዊ ሊያየው የሚገባ ፓን አፍሪካዊ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጿል። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ አሻራውን ያሳረፈበት መሆኑን ገልጾ፥ አፍሪካዊያንም ከውጭ እርዳታ ሳንጠብቅ በትብብርና በጋራ ከሰራን አህጉራችንን ማበልጸግ እንችላለን ሲልም ተናግሯል። ዎዴ ማያ አክሎም፥ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ሁለተኛው ዓድዋ ነው ማለት ይቻላል ምክንያቱም በዓድዋ ጦርነት ወቅት ኢትዮጵያዊያን ተባብረው ጠላትን ድል እንዳደረጉት ሁሉ ይህ ፕሮጀክትም አፍሪካዊያን በምዕራባዊያን ላይ የነበራቸውን ጥገኝነት ያስቀረ እና በራስ አቅም የተሰራ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑንም ነው የገለጸው። ኢትዮጵያውያን በጽናት በመቆም ተባብረው ታላቁን የአፍሪካ ግድብ ያለምንም የውጭ እርዳታ እውን በማድረግ ታሪክ መስራት መቻላቸውን መስክሯል።
በሰው ተኮር የልማት መርኃ ግብር የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች እየተሰሩ ነው
Nov 16, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦በሰው ተኮር የልማት መርኃ ግብር የከተማዋን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ መሐመድ አሚን ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዛሬ በኮምቦልቻ ሪጆፖሊታን ከተማ አስተዳደር የተከናወኑ የዲጂታል አገልግሎት ፣ የዘመናዊ የሥራ ቦታ እድሳት እና ሰው ተኮር ተግባራትን ጎብኝተዋል። የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ መሐመድ አሚን በዚሁ ወቅት፤ ስማርት ኮምቦልቻን እውን ለማድረግ በርካታ መሰረተ ልማቶች እየተገነቡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ስማርት ኮምቦልቻን እውን ለማድረግ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል የደህንነት ካሜራ ተከላ፣ የትራፊክ እንቅስቃሴ መቆጣጠሪያ እና የከተማዋን አገልግሎት አሰጣጥ ኢ-ሰርቪስ ማድረግ እንደሚገኙበት ገልጸዋል፡፡ እነዚህ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቁ ስማርት ኮምቦልቻ እውን ትሆናለች ብለዋል፡፡ ከተማዋን የማዘመን እና የነዋሪዎቿን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ ሰው ተኮር የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሰው ተኮር ስራዎች ነዋሪዎችን የስራ እድል፣ ተማሪዎችን ደግሞ የምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ከበጎ አድራጊዎች ጋር በመተባበር በ43 ሚሊዮን ብር አዲስ ቤት በማስገንባት ለአቅመ ደካሞችና ለአገር ባለውለታዎች ማስረከቡን ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይም ከተማዋን የማዘመንና የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡ መኖሪያ ቤት ከተሰጣቸው መካከል አንዷ ወይዘሮ ሰናይት ሞላ፤ የስፌት ስራ በመስራት ከሚያገኙት ገንዘብ በመቀነስ የግል ቤት ተከራይተው ይኖሩ እንደነበር በመጠቆም ቤት በማግኘታቸው እጅግ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡ በጡረታ የተገለሉት ዋና ሳጅን አበጋዝ አሊ በበኩላቸው፤ የግል ቤት ተከራይተው ይኖር እንደነበር በማስታወስ መንግስት በጨነቀኝ ሰዓት ደርሶልኛል ሲሉ ደስታቸውን አጋርተዋል፡፡ ሌላኛዋ የቤት ተጠቃሚ የሻረግ እርቅይሁን በበኩላቸው፤ መንግስት ከአስቸጋሪው የኪራይ ህይወት አውጥቶ የቤት ባለቤት እንዳደረጋቸው በመናገር ለተደረገላቸው ሁሉ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በኮምቦልቻ ለዘመናዊ አገልግሎት እና ለሰው ተኮር ተግባራት የተሰጠው ትኩረት የሚደነቅ ነው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Nov 16, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦በኮምቦልቻ ለዘመናዊ አገልግሎት እና ለሰው ተኮር ተግባራት የተሰጠው ትኩረት የሚደነቅ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ዛሬ የኮምቦልቻ ሪጆፖሊታን ከተማ አስተዳደር የዲጂታል አገልግሎትና የዘመናዊ የሥራ ቦታ እድሳትና ሰው ተኮር ተግባራትን መመልከታቸውን አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ ህንጻ የስማርት ሲቲ እሴቶችን ባሟላ መልኩ መታደሱን ገልጸዋል። ህንጻው ዲጅታል አሰራርን ለመተግበር በሚያስችል መልኩ መደራጀቱ አገልግሎትን ለማዘመን አጋዥ አቅም ይፈጥራልም ብለዋል። በተጨማሪም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ ለሚገኙ ነዋሪዎች ተገንብተው ለነዋሪዎች የተላለፉ መኖሪያ ቤቶችን መመልከታቸውን ጠቁመዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ባለሀብቶችንና ህብረተሰቡን በማስተባበር ባስገነባቸው ሁለት የመኖሪያ ብሎኮች ለአቅመ ደካሞችና አረጋውያን ደረጃቸውን የጠበቁ ቤቶችን ማስረከቡን ነው የገለፁት። በኮምቦልቻ የጎበኘናቸው የዲጂታል የከተማ አገልግሎት ፕሮጀክትና ሰው ተኮር ተግባራት በከተሞቻችን እየተገበርናቸው ያሉ የአካታች ልማት ማሳያዎች ናቸው ሲሉም ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢንስቲቲዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Nov 16, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ ኢንስቲቲዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል ሲሉም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ጽሕፈት ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት በመለወጥ መሃል ከተማ ወደ ቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሕንፃ አዛውሯል ብለዋል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የግንባታ ለውጥ እና ዘመናዊ የመሥሪያ ሥፍራ ጥበብን በማሳየት ለሠራተኞቹ እጅግ ምቹ የሆነ ስፍራንም መፍጠር ችሏል ነው ያሉት። ተቋሙ በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሕይወታችንን በፍጥነት በመቅረጽ ውስጥ ያለውን ስፍራ በሚያንፀባርቅ እና ሀገራችንም በዚህ አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ውድድር በንቁነት መሳተፏን በሚያረጋግጥ መንገድ ከፍታ ላይ ደርሷል ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ሲሆን በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል ነው ያሉት። በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ መዐከል ደግሞ ይኽንን ከባቢ የበለጠ ያጠናክረዋል ብለዋል በመልዕክታቸው። ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል። እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቅመዋል ሲሉም አስታውቀዋል።
መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ለከተሞች አገልግሎት አሰጣጥ መዘመን ትልቅ እገዛን የሚያደርግ ነው
Nov 16, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ለከተሞች አገልግሎት አሰጣጥ መዘመን ትልቅ እገዛን የሚያደርግ መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ (ዶ/ር) ገለጹ። 10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም "የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት” በሚል መሪ ሀሳብ በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡ በሁለተኛው ቀን ውሎም "የኢትዮጵያ የፐብሊክ ሰርቪስ ሪፎርም እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት" በሚል የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም የተነደፈው ለሁሉም ሴክተር ነው። እንዲሁም ዘመን ተሻጋሪ ተቋማት መገንባትን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ እሳቤው የሰራተኛን የአቅም ክፍተቶችን በመለየት የማብቃት ስራ መሆኑን አንስተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዓለምን ምርጥ ተሞክሮዎች በመውሰድ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ መተግበሩን ጠቁመዋል። ዓላማውም በከተሞች አገልግሎትን በአንድ ቦታ መስጠት እና የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ መሆኑን ተናግረዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለከተሞች አገልግሎት አሰጣጥ መዘመን ትልቅ እገዛን የሚያደርግ መሆኑን ጠቁመዋል። ስርዓቱ አካታች ለሁሉም ዜጋ ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፤ የመሶብ ዋና ማእከል በዚህ ዓመት ግንባታው እንደሚጀመር ተናግረዋል። እስካሁን 21 የመሶብ ማእከላት ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸው፤ በዚህ ዓመት 70 ተጨማሪ ማእከላት ተመርቀው ወደ ስራ እንደሚገቡ አመላክተዋል። የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንደ ሀገር የበለጸገች ሀገር የመገንባት ጥረቶች አንዱ አካል መሆኑን በመግለጽ፤ ለአገልግሎቱ የሚያስፈልጉ መሰረተ ልማቶችን ቅድሚያ ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ያስገኛል-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Nov 16, 2025 74
አዲስ አበባ፤ሕዳር 7/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አገልግሎት አሰጣጥን በማስወገድ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት ረገድ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሚና የጎላ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የደሴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር በተለያዩ መድረኮች ሕዝቡ ካነሳቸው ጉዳዮች አንዱ የአገልግሎት አሰጣጣችሁን ፈትሹ፤ ከእጅ መንሻ ነጻ የሆነ አገልግሎት ልናገኝ ይገባል የሚል ነበር ሲሉ አውስተዋል። በዚህም መሠረት በተቋማት የሚስተዋሉ ብልሹ አገልግሎት አሰጣጦችን በማስወገድ ዘመኑን የዋጀና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ወደ ሥራ እያስገባን ነው ብለዋል። አስተዋዩ የደሴ ሕዝብ ልማት ፈላጊ፣ ለፍትሕ የቆመ፣ በውይይት የሚያምን፣ በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራና የጸና መሆኑንም በንግግራቸው አንስተዋል። ደሴ ከተማ በከፍተኛ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ እንደምትገኝ ተመልክተናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን የልማት ጉዞ በማሳለጥ ረገድ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት የጎላ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት፣ ከዚህ በፊት በማንዋል ይሰጥ የነበረውን የመንግሥት አገልግሎት በዲጂታል ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እንግልት የሚቀንስ መሆኑንም አስረድተዋል። ተገልጋዮች ጊዜያቸውን፣ ገንዘባቸው ብሎም ጉልበታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ በማድረግ ረገድ መሶብ የአንድ ማዕከል ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ገልጸዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከሲቪል ሰርቪስ ማሻሻ ሪፎርሞች ውስጥ አንዱ አካል እንደሆነ ገልጸው፤ በሕዝብና በመንግሥት መካከል ያለውን ጥብቅ ቁርኝት ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሳድግ መሆኑን ጠቅሰዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በይበልጥ ማስፋፋትና ማጠናከር እንደሚገባም አሳስበዋል። በሌላ በኩል የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ወደ ሁሉም አካባቢዎች መድረስ እንዳለባቸው ተናግረዋል። ጽዳትና ውበት የደሴ መገለጫዎች ሊሆኑ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህ ደግሞ የከተማዋ ነዋሪዎች በተለይም የንግዱ ማኅበረሰብ ግብሩን በወቅቱና በታማኝነት መክፈልና ተጨማሪ አስተዋጽኦም በግሉ ማበርከት እንደሚጠበቅበት አመላክተዋል። የኮሪደር ልማትና የኢትዮጵያን ብልጽግና በሚፈለገው ልክ ለማሳካት እያንዳንዱ ማኅበረሰብ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። ሰላምና ልማት ተመጋጋቢ በመሆናቸው ሕዝቡ ሰላሙን ማስጠበቅ እንዳለበትም በንግግራቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ህዝቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለውን ቅሬታ በዘላቂነት ይፈታል
Nov 15, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ህዝቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለውን ቅሬታ በዘላቂነት እንደሚፈታ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የደሴ ከተማን መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት አስጀምረዋል፡ ፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ደሴ ከተማ በሀገረ መንግሥት ግንባታ ዘመን ተሻጋሪ ገድል የጻፈች፣ የሰለጠነ ማህበረሰብ የገነባች፣ የዘመናዊ መገለጫ ከተማ መሆኗን ገልጸዋል፡፡ ህዝቡ አስተዋይ፣ ለፍትህ የቆመ፣ በውይይት የሚያምን፣ የሰላም አምባሳደር የልማት አርበኛ በኢትዮጵያዊነቱ የማይደራደር መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የወሎ ምድር ለኢትዮጵያዊነት የመደመር ቅኝት ማሳያ፣ ድንቅ እሴት እንደ ቦርከና ወንዝ ሞልቶ የሚፈስበት የአብሮነት እና የመዋደድ ተምሳሌት መሆኑንም አንስተዋል፡፡ ወሎ የጥበብ መፍለቂያና የዕውቀት ማዕድ መሆኗን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የወሎዋ ዕምብርት ደሴ ከተማ አሁን በከፍተኛ የልማተ እንቅስቃሴ ላይ ትገኛለች ብለዋል፡፡ የደሴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በከተማዋ የተጀመረውን የልማት ጉዞ ለማሳለጥ የጎላ አበርክቶ እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢኒሼቲቭ የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በተለያዩ አካባቢዎች በማንዋል ሲሰጥ የቆየውን የመንግሥት አገልግሎት በአንድ ማዕከል ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የተገልጋዮችን ጊዜና ጉልበት በመቆጠብ በህዝብና መንግሥት መካከል ያለውን ጥብቅ ቁርኝት ወደ ተሻለ ደረጃ እንደሚያሳድግ ገልጸዋል፡፡ ብልሹ አሰራርን በማስወገድ ዘመኑን የዋጀና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችል ገልጸው፤ በደሴ ከተማ የተሰራው ማዕከል የህዝቡን የረጅም ጊዜ የፈጣን አገልግሎት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በለውጡ መንግሥት ደሴ የብልፅግና ብርሃን ወጋገን ፈንጥቃለች፣ ለኗሪዎቿ ምቹ የበለፀገች እና የተዋበች ከተማ መሆን የሚያስችላትን የተስፋ ጎዳና ጀምራለች ብለዋል፡፡ የመጀመሪያው ምዕራፍ የደሴ የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውበት እየገለጠ መሆኑን በመጥቀስ፤ ለተሻለ አፈጻጸም ህዝቡና አመራሩ ተጋግዞ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ ሰላምና ልማት ተመጋጋቢ መሆናቸውን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተጀመረው ልማት ከግብ እንዲደርስ ህዝቡ የሰላም ዘብነቱን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡
ስፖርት
አርባምንጭ ከተማ በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ድሉን አስመዘገበ
Nov 16, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስድስተኛ ሳምንት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ መሰረት ማቴዎስ እና መድኃኒት ዓለሙ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ወርቅነሽ መለሰ ለባህር ዳር ከተማ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ውጤቱን ተከትሎ አርባምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል። ቡድኑ በአራት ነጥብ ደረጃውን ከ14ኛ ወደ 12ኛ ከፍ በማድረግ ከወራጅ ቀጠና ወጥቷል። በውድድር ዓመቱ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ባህር ዳር ከተማ በአራት ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ቀን ላይ በተደረገ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ልደታ ክፍለ ከተማን 4 ለ 0 አሸንፏል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የስድስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል።
ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ መድንን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሁለተኛ ከፍ አደረገ
Nov 16, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሃ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የኢትዮጵያ መድን ተከላካይ ንጋቱ ገብረስላሴ በ18ኛው ደቂቃ በራሱ ላይ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በውድድር ዓመቱ አራተኛ ድሉን ያስመዘገበው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ12 ነጥብ ተመሳሳይ ነጥብ ባለው የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በግብ ክፍያ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሊጉ የመጀመሪያ ሽንፈቱን ያስተናገደው የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በአምስት ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ከግብጹ ፒራሚድስ በነበረበት የማጣሪያ ጨዋታ የተራዘመ መሆኑ ይታወቃል። መድን ቀሪ ተስተካካይ ጨዋታውን በቀጣይ ከሸገር ከተማ ጋር ያደርጋል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ ያደረገበት ድል አስመዘገበ
Nov 16, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ልደታ ክፍለ ከተማን 4 ለ 0 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መሳይ ተመስገን ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ምርቃት ፈለቀ እና እፀገነት ግርማ ቀሪዎችን ጎሎች አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች እየቀሩት በ12 ነጥብ ደረጃውን ከአምስተኛ ወደ ሶስተኛ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሶስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ልደታ ክፍለ ከተማ በአምስት ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በአሁኑ ሰዓት ባህር ዳር ከተማ ከአርባምንጭ ከተማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው።
በሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ መድን የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Nov 16, 2025 76
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 7/ 2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሃ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ መድን ዛሬ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል። በአዲስ አበባ ስታዲየም የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና የወቅቱ የሊጉ ዋንጫ ባለቤት ኢትዮጵያ መድን የሚያደርጉት ጨዋታ የተመልካቾችን ትኩረት ስቧል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ሽንፈትን አስተናግዷል። በጨዋታዎቹ አምስት ግቦችን ሲያስቆጥር ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ቡዱኑ በዘጠኝ ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ መድን በበኩሉ በውድድር ዓመቱ ባደረጋቸው ሶስት ጨዋታዎች አንድ ጊዜ ድል ሲቀናው ሁለት ጊዜ አቻ ተለያይቷል። ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ አንድ ግብ ተቀጥሮበታል። መድን በአምስት ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። ሁለቱ ቡድኖች በ2017 ዓ.ም በሊጉ ያደረጓቸው ሁለት ጨዋታዎች በተመሳሳይ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል። የቡድኖች ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ከግብጹ ፒራሚድስ ጋር በነበረው የሁለተኛ ዙር ማጣሪያ ምክንያት የተራዘመ ነው። ኢትዮጵያ መድን በቀጣይ በሚገለጽ ቀን እና ቦታ ከሸገር ከተማ ጋር ቀሪውን ተስተካካይ ጨዋታ እንደሚያደርግ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ (ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃ ላላት ጽኑ ቁርጠኝነት እውቅና የሰጠ ነው - ኢጋድ
Nov 15, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃና አረንጓዴ ልማት ቁርጠኝነቷ እውቅና የሰጠ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ገለጸ። የድርጅቱ ዋና ጸሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ኮፕ 32 እንድታዘጋጅ መመረጧን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤውን ማዘጋጀቷ በአየር ንብረት እና ልማት ያላት መሪነት እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። የአካባቢ ስነ ምህዳርን ወደ ነበረበት የመመለስ፣ ዘላቂ እድገትና የማይበገር አቅም ለመገንባት ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያመላክትና ለዚህም ስራዋ እውቅና የሰጠ መሆኑን አመልክተዋል። አረንጓዴ ዐሻራ እና የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ስራ ማሳያዎች እንደሆኑም ነው የተናገሩት። ኮፕ 32 ለኢጋድ ቀጣና ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸው ተቋሙ ድርቅ፣ የአየር ንብረት ለውጥ የፈጠረው የዜጎች መፈናቀልና የውሃ እጥረትን ጨምሮ ሌሎች አንገብጋቢ አጀንዳዎች የበለጠ ትኩረት እንዲሰጣቸው እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ኢጋድ ከኢትዮጵያ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ማዕቀፍ ጽህፈት ቤት(UNFCCC Secretariat) እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን ጉባኤው ሁሉን አሳታፊ፣ የአፍሪካ የቅድሚያ ትኩረቶች ማዕከል ያደረገና ለአየር ንብረት ለውጥ ዘላቂ መፍትሄ የሚገኝበት እንዲሆን በትብብር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በብራዚል ቤለም እየተካሄደ የሚገኘው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 30) ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን ኮፕ 32 ጉባኤ እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል። የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ሙሉ ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ ነው - የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር
Nov 15, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀ መንበሩ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ32)ን እንድታስተናግድ በመመረጧ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጉባኤውን የማስተናገድ ውሳኔው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ መሆኑን ሊቀመንበሩ ገልጸው ይህም አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃ ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አማካኝነት እያሳየች ያለውን የአየር ንብረት የመሪነት ሚናም አድንቀዋል። ኢትዮጵያ መጠነ ሰፊ የደን መልሶ ልማት እና አረንጓዴ ዐሻራን ጨምሮ ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ እርምጃዎችን እየወሰደች እንደምትገኝ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ እምቅ አቅም እንዳላት አንስተው ከፍተኛ ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ጉባኤዎችን ለማዘጋጀት ጠንካራ ተቋማዊ አቅም እና ልምድ አላት ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ ጉባኤውን እንድታስተናግድ መመረጧ በዓለም አቀፍ ትብብር ያላትን ማዕከላዊ ሚና የበለጠ እንደሚያሳድገውም ገልጸዋል። ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ማዕቀፍ(UNFCCC) እና አጋሮች ጋር በመሆን(ኮፕ 32) ሁሉን አካታችና ውጤታማ በማድረግ የአፍሪካን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የበለጠ ለማራመድና ዓለም አቀፍ አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። በብራዚል ቤለም እየተካሄደ የሚገኘው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 30) ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚከናወነውን ኮፕ 32 እንድታስተናግድ ተመርጣለች። የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ሙሉ ድጋፋቸውን መስጠታቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ውጤት ለማምጣት ቁርጠኛ ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 14, 2025 123
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አረጋገጡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ይቀጥላል
Nov 12, 2025 147
አዲስ አበባ፤ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አስር ቀናት በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፥ በሰሜን፣በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ፣ መካከለኛው እና ደቡብ ደጋማ አካባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ እንደሚቀጥል አስታውቋል። በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑት የደቡብ፣ደቡብ ምስራቅ እና የደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች ያሳሉ ብሏል። ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ በሰሜን፣ መካከለኛው፣ ምዕራብና ደቡብ ጎንደር ዞኖች፣ባህርዳር ዙሪያ፣ አዊ፣ በምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ መተከል፣ አሶሳ፣ ካማሺ፣አርሲ፣በባሌ ዞኖች አልፎ አልፎ ሊዘንብ እንደሚችል ኢኒስቲትዩቱ ገልጿል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት በደቡብ ምዕራብ እና ደቡባቢ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚኖረው መካከለኛ መጠን ያለው ርጥበት ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅስቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው አስታውቋል። የበጋ ርጥበት ተጠቃሚ ተፋሰሶች መጠነኛ የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን የተቀሩት ዝቅተኛ ርጥበት እንደሚኖራቸው ገልጿል። በዚህም አብዛኛው ባሮ አኮቦ፣ መካከለኛው እና ታችኛው ኦሞ ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ አባይ እንዲሁም ገናሌ ደዋ መካከለኛ ርጥበት ያገኛሉ፡፡ አብዛኛው አዋሽ፣ዋቤ ሸበሌ፣አፋር ደናክል፣ተከዜ፣ ኦጋዴን ደግሞ ከመጠነኛ ርጥበት እስከ ደረቅ ሁኔታ ይኖራቸዋል ተብሏል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 450
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 602
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 498
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Oct 24, 2025 751
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 96
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 286
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው። በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው። የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል። በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 356
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 529
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2071
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2323
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3203
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3294
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 1340
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 905
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6742
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5216
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
በጥምር ግብርና ስኬት ያስመዘገቡት አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ
Nov 14, 2025 203
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ - ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ጨዛ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ለዘመናት ባከናወኑት የግብርና ልማት ሥራ ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ የዘለለ አልነበረም። ዛሬ ላይ ሆነው ያን ዘመንና ያሳለፉትን ዕድሜ ሲያስታውሱ ይቆጫሉ። በኋላ ቀር መንገድ ሲያከናውኑት ከነበረው የግብርና ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆንም፤ ሀብት ማፍራትም ሳይችሉ ቀርተዋል። አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ይባላሉ። ከሰበሰቡት ሰብል ጎተራቸው ሳይጎድል፣ ከእንስሳት እርባታ ስራቸውም ጥገታቸው ሳትነጥፍ ማየት የዘውትር ህልማቸው ነበር። ለም መሬት ይዘው ምርታማ ባለመሆናቸው ሲቸገሩ፣ የሚሰራ ጉልበት ይዘው ማዕዳቸው እየጎደለ የጎልማሳነት ዕድሜ መባቻ ድረስ ችግር ሲፈራረቅባቸው ዓመታትን አሳልፈዋል። ይህ ፍላጎታቸው ሰምሮ፣ ጓሯቸው ለምቶ፣ ቤታቸው ሞልቶና ጥሪት አፍርተው የማየት ውጥናቸው ሳይሳካ ዓመታት ቢቆጠሩም ዛሬ ግን በጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ነገሮች ተቀይረዋል። የዓመታት ምኞታቸውን ማሳካት ጀምረዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ለስኬት እንዲበቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢያቸው አርአያ የሆኑ አርሶ አደር አድርጓቸዋል። የጥምር ግብርና ስራቸው ለዓመታት ከነበሩበት ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ በማውጣት ለአፍም ለኪስም ሆኗቸዋል። የመንግስት የልማት ትኩረት የሆነው ጥምር ግብርና በውስን መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅንጅት እንዲያለሙ እድል ፍጥሮላቸዋል። በዋናነት በሰብል፣ በእንሰት፣ በፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ላይ አተኩረው እየሰሩ ይገኛሉ። ይህም የአንዱ ክፍተት በሌላው እየተሞለ ውጤታማ ስላደረጋቸው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው። ለቤት ፍጆታ ብቻ ያመርቱ የነበረው የእንሰት ምርትን በማስፋፋት ችግኙንና ተረፈ ምርቱን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጭምር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያመርቱት ገብስ ለሌሎች አርሶ አደሮች ምሳሌ መሆን ችለዋል። ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ስለሚያረቡም ወተት ከማጀታቸው አይጠፋም። በጓሯቸው የሚያለሙትን አትክልትና ፍራፍሬ ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል። አርሶ አደሩ ከንብ ማነብ ሥራቸውም እንዲሁ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው። ከአካባቢው ስነምህዳር ምክንያት ብዙም ያልተለመደውን ቡና በመትከል ለፍሬ አብቅተዋል። የእሳቸውን ፈለግ የተከተሉ ሌሎች አርሶ አደሮችም ቡና ማልማት ጀምረዋል። በእጅ ያለን ሀብት ወደ ውጤት ለመቀየር ተግቶ መስራትና ጽናት ያስፈለጋል ያሉት አርሶ አደር ወልዴ፣ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ሙያዊ ድጋፍና የተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ለውጤታቸው ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የእርሻ ልማትና የእንስሳት እርባታውን በቅንጅት ማከናወናቸውም እንዲሁ። አርሶ አደር ወልዴ የዓመታት ቁጭታቸው ዛሬ መፍትሄ እያገኘ ነው። የጥምር ግብርና ሥራቸው በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉና ልጆቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል። መኖሪያ ቤትን ጨምሮ የተለያየ ሀብት ለማፍራት ምክንያት በመሆኑም ልማቱን አስፋፍቶ ለማከናወን አቅደዋል። አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጭምር አርአያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙራዱ ብሩ ናቸው። ቀደም ሲል በገብስ ምርት ላይ ብቻ አተኩረው ይሰሩ የነበረውን የግብርና ሥራ እንዲቀይሩ ምክንያት እንደሆኗቸው ይገልጻሉ። ከአርሶ አደር ወልዴ በወሰዱት ልምድ ወደ ጥምር ግብርና ገብተዋል። በዚህም ድርቅ የመቋቋም አቅም ያለውን እንሰት በማሳቸው በስፋት ማልማት ጀምረዋል። የነበሯቸውን ሀገረሰብ የዳልጋ ከብቶች በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በመቀየር የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው እየሰሩ ነው። ጥምር ግብርና የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ከአርሶ አደር ወልዴ ተምሪያለሁ ይላሉ። ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባለፈ የመሬት ለምነትን ለማስጠበቅም ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ የጀመርነውን ሥራ እናጠናክራለን ሲሉም ነው የገለጹት። የሙህር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ መኑር ጀማል በበኩላቸው "አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ በውስን መሬት ገብስ፣ እንሰት፣ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በጥምር በማልማት የራሳቸውን ህይወት ከመቀየር ባለፈ ለሌሎች አርሶ አደሮች አርአያ እየሆኑን ነው ብለዋል። አርሶ አደሩ በሽታ መቋቋም የሚችሉና ለመድሃኒትነት የሚፈለጉ የእንሰት ዝርያዎችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ በመጥፋት ላይ የነበሩ የእንሰት ዝርያዎችን የመታደግና የአፈር ለምነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የጥምር ግብርና አሰራር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ በመሆኑ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት። የአርሶ አደር ወልዴ ልምድን በማስፋት የሌሎች አርሶ አደሮችም ጓዳ ሞልቶ እንዲትረፈረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጥምር ግብርና አርሶ አደሩ ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ጭምር እንዲተርፍ የማድርጉ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል። ልማቱ እርስ በእርስ የሚደጋገፉና በአንድ መሬት ላይ የተለያዩ ምርቶችን በማግኘት የተሻለ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚሰራው ሥራ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ በጥቂት መሬት ብዙ ማምረት መቻል ነው። በመሆኑም በተለይ የመሬት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በሥራ ውጤታማ ለመሆን ሁሉም ነገር ምቹና አልጋ በአልጋ መሆን የግድ እንዳልሆነ አርሶ አደሩ ጥሩ ማሳያ ናቸው። ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ዕድል እንዴት ወደሀብትነት መቀየር እችላለሁ ብለው ከሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ የእሳቸው የስኬት ጉዞ በቂ ማሳያ ነው። ሰርቶ ለመለወጥም ሆነ ሀብት ለማፍራት ችግሮችን በጽናት ማለፍ እና የሥራ ትጋት ወሳኝ ነውና ተሞክሯቸውን ማስፋት ያስፈልጋል።
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ"
Nov 12, 2025 297
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ" ብርሃኑ ፍቃዱ -ከሰቆጣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ማብራራታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችበትን የ30 ዓመታት ታሪክ ለመቀልበስ ይህን ያህል ዓመት እንደማይወስድ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ተቋማዊ መሰረት የሌለው የሚያስቆጭ ብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል ስለመሆኑም አንስተዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ እና አቶ አድማሱ ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር የተወለዱበት ስፍራ፣ የኖሩበት ቀዬ፣ ያሳደጋቸው ማህበረሰብ ... የዘመናት ትዝታና ትውስታቸው እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህን የታሪካቸው አካል የሆነውን የባሕር በር ማጣትም የሁል ጊዜ ፀፀትና እንደ ሰውነት ጥላ አብሮዋቸው የሚዞር እውነታ ነው። ከአካባቢው ርቆ ለሚገኝ ሰው ትውስታውን ሲያወራ ለሌላው ተረት ተረት፤ ለራስ ደግሞ የውስጥ ቁስል ማገርሸት ሆኖ ነው የሚሰማው ይላሉ። ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብንና የቀይ ባህር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሸፍጥ ማጣቷ በቀይ ባህር ላይ እየዋኙ፣ ውሃ እየተራጩ፣ በዳርቻው ነፋሻማ ስፍራ እየተዝናኑ... ለኖሩት ለእነ መለሰ እና አድማሱ መቼም የማይረሳ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ለአለም ማሕበረሰብ ጥያቄውን ሲያሳውቁ ተደብቆ ለቆየው ትውስታቸው አዲስ ተስፋ እንደሰጣቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለ12 ዓመታት እንዳገለገሉ በትውስታና ቁጭታቸውን ወደ ኋላ ተመልሰው ያወሳሉ። አሁን በሰቆጣ ከተማ የሚኖሩት አቶ መለሰ ይሄይስ ፤ የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ተደማሪ አቅም ነበር በወቅቱ ይላሉ። ይህን የአሰብ ወደብንና የቀይ ባሕር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሴራ ኢትዮጵያ ስታጣ ይሰሩበት ከነበረው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ስራ አቁመው ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሰቆጣ መምጣታቸውን አውስተዋል። በራሳቸው ላይ ከደረሰባቸው የስራ እና ሃብትና ንብረት ማጣት ፣ እንግልትና ሌሎች ችግሮች በላይ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተነጠለችበትን ሁኔታ ሲያስቡና ሲያሰላስሉ እንደሚያስቆጫቸው ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን በማጣት የባሕር በር ብቻ ሳይሆን የገቢና ወጭ ንግድን፣ የነዳጅ ማጣሪያ ጭምር ነው ያጣችው ያሉት አቶ መለሰ፤ አሁን ጥያቄው መነሳቱ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ገናናነቷ ለመመለስ ያለመ አበረታች ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። መንግስት ያነሳው የባሕር በር ጥያቄም የዘመናት ቁጭታችንን፣ ብስጭታችንን እና ህልማችንን ከተደበቀ ትውስታ፤ ወደ አዲስ ተስፋ የወሰደ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ህጋዊና ታሪካዊ ነው ያሉት አቶ መለሰ ፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝም ለአዲሱ ትውልድ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። ከ1973 ዓ.ም ጀምረው ለአስር ተከታታይ ዓመታት በአሰብ ወደብ የሲቪል መሃንዲስ ክፍል ሰራተኛ እንደነበሩ ያወሱት አቶ አድማሱ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባሕር ባር ባለቤት በሆነችባቸው ዘመናት ገናና እና የተከበረች ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል። የባሕር በሩ የኢትዮጵያ የገቢና ወጭ ንግድ የሚሳለጥበት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሄን ታላቅ ትሩፋትና ፀጋ ለማስመለስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ቁጭትና ትውስታችንን ወደ አዲስ ተስፋ የቀየረ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶችና ባንዳዎች እኩይ ሴራ የባሕር በር ካጣች ወዲህ ጥያቄውን ማንሳት የማይቻልበት የአፈናው ዘመን አክትሞ በለውጡ መንግስት መነሳቱ አበረታችና ለማስመለስም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ ስለባሕር ባር አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ለስኬታማነቱ የድርሻዬ እወጣለሁ ሲሉም ገልጸዋል።