ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን ለህብረተሰቡ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስችሏል
Jun 7, 2026 44
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎች ገለጹ፡፡ መንግስት በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ እያደረጋቸው ያሉ ሁለንተናዊ ማሻሻያዎችና በመዲናዋ የተገነቡት ዘመናዊ የአውቶብስ ፌርማታዎች ለአገልግሎቱ መቀላጠፍና ለተሳፋሪዎች ምቾት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው፡፡ በመዲናዋ ደረጃቸውን በጠበቁና ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ለማህበረሰቡ የተሳለጠ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ገቢራዊ ተደርጓል፡፡ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ በሚገኙ ከተሞች ሳምንቱን ሙሉ ያለማቋረጥ የትራንስፖርት አገልግሎት በማቅረብ ላይ ያሉት የከተማ አውቶብሶች ለነዋሪዎች ኢኮኖሚዊና ማህበራዊ እፎይታን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑት አቶ መኮንን ለገሰ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የብዙሃን ትራንስፖርት ከሌሎች አማራጮች አንጻር አነስተኛ ታሪፍ ያለው በመሆኑ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ትልቅ አቅም ይፈጥራል፡፡ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳ የሚንቀሳቀሱ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይሄውም ያለ ምንም እንግልት በሰዓታቸው የሥራ ቦታቸው ላይ እንዲገኙ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡ ገቢያቸውን ያማከለና ተመጣጣኝ የትራንስፖርት አገልግሎት ከማግኘት ባለፈ ለሥራቸው መቃናትና ምርታማነት የጎላ አበርክቶ እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ መስከረም ዳመነ፤ አገልግሎቱ በየጊዜው እየተሻሻለ በመምጣቱ ጠዋትም ሆነ ማታ ፈጣን፣ ምቹና ቀልጣፋ ግልጋሎት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን የነዋሪዎች የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ በማሳለጥ ገንቢ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡ የከተማ አውቶብስ አሽከርካሪዎች በበኩላቸው ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገው አዲሱ አሠራር በሥራቸው ላይ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ አቶ ያለው ነጋ በትራንስፖርት ዘርፉ የተተገበረው ሪፎርም በካሜራና ጂፒኤስ (GPS) የታገዘ ዘመናዊ አሰራርን በማምጣት የአሽከርካሪዎችን የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደጉን ገልጸዋል፡፡ ቴክኖሎጂው ቀደም ሲል በፌርማታዎች ይስተዋሉ የነበሩትን ሰልፎች በማስቀረት በመዲናዋና ከዙሪያ ከተሞች ለሚመጡ ተጠቃሚዎች ተመራጭ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላኛዋ አሽከርካሪ ወይዘሮ ፍሬህይወት ኤካ፤ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን በተለይ ርቀት ላላቸው መስመሮች ከታሪፍ አንፃር እጅግ አዋጭ ነው ብለዋል፡፡
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ የተያዘው ዕቅድ በስኬት የተፈፀመበት ነው -አቶ አደም ፋራህ
Jun 7, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገራዊ ግቦቹን እንዲያሳካ እና ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ በብልጽግና ፓርቲ የተያዘው ዕቅድ እና የተከናወኑ ዐበይት ተግባራት በስኬት የተፈፀሙበት መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። አቶ አደም ፋራህ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ላለፉት ሁለት ቀናት በሶማሌ ክልል ሸቤለይ ሪዞርት ከፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር እስከ ምርጫው ዕለት ያለውን የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ሥራዎች ዕቅድ አፈፃፀም በጥልቀት በመገምገም እና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ላይ በመግባባት መድረኩ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ለምርጫው ስኬታማነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፌዴራል እና የክልል ፀጥታ ኃይሎች፣ በታዛቢነት የተሳተፉ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ ተቋማት እንዲሁም ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በማሳየት ከለሊቱ 10 ሰዓት እስከ ሚቀጥለው ለሊት 10 ሰዓት ድምፅ ለመስጠት የተሰለፈው እና ለምርጫው ስኬት የሚችለውን ሁሉ ላደረገው ለተከበረው ሕዝብ፣ እንዲሁም ሌሎች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ ምስጋናችንን አቅርበዋል። ከግምገማዊ ውይይት መድረኩ ጎን ለጎን፣ የስብሰባው ተሳታፊ ከፍተኛ አመራሮች በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ በጅግጅጋ እየተከናወኑ ያሉ ዐበይት የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም በክልሉ መንግሥት እና በሕዝቡ ጥረት እየተመዘገቡ ያሉ አንጸባራቂ ስኬቶችን በተጨባጭ መመልከታቸውን ነው የገለጹት። የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራዎች የከተማዋን ገጽታ ሙሉ በሙሉ የቀየሩ፣ የተቀናጁ መሠረተ ልማቶችን ያሟሉ እና ፈጣን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን የፈጠሩ ናቸው ብለዋል አቶ አደም። ይህ ሥራ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን እና ከተማዋን የቀጣናው የልማት እና የንግድ ማዕከል እንድትሆን እንዳደረጋትም ጠቁመዋል። በክልሉ መንግሥት ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃውን አዲስ የፖሊስ ሆስፒታል ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሚሰጠው አገልግሎት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በተለይም የፖሊስ አባላት እና ቤተሰቦቻቸው የሚያገኙትን የጤና አገልግሎት በማላቅ፣ የፀጥታ ኃይሎች ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን በላቀ ሞራል እና ቁርጠኝነት እንዲወጡ የሚያግዝ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ነው ያሉት። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ትኩረት የሕዝብን አገልጋይነት ማረጋገጥ እና የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን ነው ያሉት አቶ አደም ፋራህ፣ በመላው ኢትዮጵያ የተገነቡት እና ግንባታቸው እየተጠናቀቀ ያሉት የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት የቢሮክራሲ ማነቆዎችን በመቅረፍ የዜጎችን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ እያሳደጉ እንደሚገኙም ገልጸዋል። በአጠቃላይ በጅግጅጋ የተመለከቱት ፈጣን እና ሁለንተናዊ ለውጦች የብልጽግና ፓርቲን የልማት እና የመልካም አስተዳደር እሳቤዎች እንዲሁም ፖሊሲዎች ውጤታማነት በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውን አስምረውበታል። ከተማዋ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገች ያለችበት አግባብ እጅግ የሚያስደስት፣ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ ምሥል ያየንበት እና ለሌሎች አካባቢዎችም አርአያ የሚሆን ነው ሲሉም ገልጸዋል። በከፍተኛ ትጋት እና ቁርጠኝነት እውነተኛ ዴሞክራሲን ከተጨባጭ የልማት፣ የመልካም አስተዳደር እና የሰላም ስኬቶች ጋር በማጣመር፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና በተግባር የማረጋገጥ ስኬታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር አሳይተዋል
Jun 7, 2026 126
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየታቸውን የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎችም እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ መካሄዱ ይታወቃል። ኢትዮጵያዊያን በመረጡበትና ኢትዮጵያም ባሸነፈችበት ምርጫ የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ አስተምህሮና ታዛቢነት የነቃ ተሳትፎ አድርገዋል። የምርጫ ሂደቱን በማስመልከትም የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌደሬሽንና የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር የሥራ ኃላፊዎች ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አሕመድ ሁሴን እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈጸም አቅም በተግባር የታየበት ነው። በምርጫውም በምርጫ አስተምህሮና ታዛቢነት በርካታ አባላትን በማሰማራት የሂደቱን ዴሞክራሲያዊነትና አሳታፊነት ማረጋገጥ የሚያስችል ተሳትፎ ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያንና የፖለቲካ ፓርቲዎች ነጻ፣ ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና በሁሉም መለኪያ የነቃ ተሳትፎ ያደረጉበት መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ተናግረዋል። ይህም ኢትዮጵያዊያንና የፖለቲካ ፓርቲዎች ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ መሰረት በመጣል ቁርጠኝነታቸውን በተግባር ያሳዩበት መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር መስዑድ ገበየሁ በበኩላቸው፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሰከነ ተሳትፎ የታየበትና ሰብዓዊ መብቶችን ያከበረ ነበር ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሃሳባቸውን ለህዝብ ባቀረቡበት ወቅት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጨምሮ በብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ የነበራቸው ትብብር አስደማሚ እንደነበር መታዘባቸውን ገልጸዋል። በምርጫ ወቅት በነበረው ትዝብትም ምርጫ ጣቢያዎች ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መራጮች ምቹና ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በተሟላ ሁኔታ የተጠቀሙበት ሁኔታን ፈጥሮ እንዳለፈ ገልጸዋል። በተጨማሪም የዘንድሮው የምርጫ ሂደት ከሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አንጻር በጥሩ ደረጃ ላይ የተከናወነና ስኬታማ እንደነበር አስታውቀዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ወጣቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር በመጠቀም የነቃ ተሳትፎ አድርገዋል ያለው ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ተወካይ አሌክሳንደር ንጉሴ ነው። በምርጫ ሂደቱ የነበረው የወጣቶችና የፖለቲካ ፓርቲዎች የነቃ ተሳትፎም ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጿል። በሂደቱ የፌዴሬሽኑ ታዛቢዎች ከተለያዩ የፖለቲካ ፖርቲዎች ተወካዮች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ከምርጫ አስፈፃሚዎች ጋር በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን በብቃት እንደተወጡ ተናግሯል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት እናታለም እንዳለ በበኩላቸው፤ በምርጫው ሂደት ሴቶች የነበራቸው ንቁ ተሳትፎ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝት በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። በሂደቱም በርካታ ሴቶች በምርጫ ታዛቢነትና በመራጭነት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብታቸውን በተግባር እንዲጠቀሙ ማድረግ እንደተቻለ አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን የሚተኩ እና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶች በስፋትና በጥራት እንዲመረቱ አስችሏል
Jun 7, 2026 161
ኮምቦልቻ ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ምርትን በመተካትና ለውጭ ምንዛሬ ግኝት የሚሆኑ ምርቶችን በጥራትና በስፋት በማምረት ረገድ ለዘርፉ እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለፁ። «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው የአማራ ክልል ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በኮምቦልቻ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንደገለጹት፤ ንቅናቄው ባለፉት ዓመታት የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማሳደግና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ከፍተኛ ሚና አበርክቷል። ሚኒስትሩ አክለውም፣ በንቅናቄው አማካኝነት ኢንዱስትሪዎችን መደገፍ፣ መሠረተ ልማቶችን ማሟላት፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና በተግዳሮቶች ላይ መፍትሔ መስጠት መቻሉን ገልጸው፤ በእነዚህም ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል። በተጨማሪም ንቅናቄው የገቢ ምርቶችን ከመተካትና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶችን በጥራትና በብዛት ከማምረት ባሻገር፣ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቻሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል። በአማራ ክልልም ንቅናቄው በርካታ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩና አዳዲስ ባለሃብቶችም በኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፤ በክልሉ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተቻለ ሲሆን፣ ይህም የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ንቅናቄው የገቢ ምርቶችን በመተካትና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረት ረገድ ካስገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር፣ ማኅበረሰቡ በሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀምና በራሱ ምርት የመኩራት ባሕል እንዲያዳብር ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ተናግረዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጣይም ዘርፉን የመደገፍ፣ የማዘመንና የማስፋት ሥራዎችን በማጠናከር ይበልጥ ተጠቃሚ ለመሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። አክለውም የክልሉ መንግሥት ለዚህ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ በበኩላቸው፤ በንቅናቄው አማካኝነት ባለፉት አራት ዓመታት 496 የሚሆኑ አዳዲስና ነባር ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፉ ከ125 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል። አቶ እንድሪስ አክለውም፤ በንቅናቄው አማካኝነት ከባለሀብቶች ጋር በቅርብ በመሥራት ምርቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የብድር አቅርቦት እንዲያገኙ፣ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉላቸው እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያገኙ መቻሉን ገልጸዋል። በመርሐግብሩ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት የምርምርና የማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jun 7, 2026 132
ሰመራ፣ግንቦት 30/2018(ኢዜአ):-ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የሚከናወኑ የምርምር ሥራዎችንና የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ገለጹ። ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ደግሞ በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ የሚገኝ አሳሳቢ ክስተት ነው። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መንግሥትና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ችግሩን ለመግታት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ። በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያላቸውን የምርምር አቅምና የማኅበረሰብ አገልግሎት ድርሻ በመጠቀም፣ የሕገ-ወጥ ዝውውርን መነሻ ምክንያቶች ለይቶ ማውጣትና ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ ላይ ሰፊ ኃላፊነት እንዳለባቸው ይታመናል። በዚሁ ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች እንደገለጹት፤ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የሚከናወኑ የምርምር ሥራዎችና የማኅበረሰብ አገልግሎቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የህግና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኀላፊ ቹዌል ኦኬደ እንዳሉት ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርና ፍልሰትን ከመከላከል አኳያ የተለያዩ ተግባራት በቅንጅት ተከናውነዋል። ስልጠናዎችን በማዘጋጀት በአካባቢው በሚገኙ አምስት ቋንቋዎች ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ለአብነት አንስተዋል። የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ኃላፊ አቶ አብርሃም ክንፈ፤ ዩኒቨርሲቲው ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመከላከል ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎት መስጠቱን አስታውቀዋል። ማዕከላቱ በተለያዩ አካባቢዎች የሕግ ቢሮዎችን በመክፈት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን እንደሚሰጡ ገልጸዋል። በተጨማሪም ተጎጂዎች የሕግ ውክልና እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ፣ የሰብአዊ መብት አያያዝን የተመለከቱ ተግባራትን የማስተባበር ሥራ እንደሚያከናውኑ ተናግረዋል። የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የህግና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኀላፊ ሳለአምላክ አታላይ እንዳሉት ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል በክልሉ ከሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው። የምርምርና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በማዘጋጀትና የህግ ድጋፍ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። መንግሥት መደበኛ ያልሆነ የዜጎችን ፍልሰትና ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በማስቀረት፣ ዜጎች ሕጋዊ አሠራርን ተከትለው መሥራት የሚችሉበትን ዕድል እያመቻቸ እንደሚገኝ የገለጹት ደግሞ የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዘካሪያስ ኤርኮላ(ዶ/ር) ናቸው። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት የሚመራበትን ሕግ እንዲሁም የፍትሕ ሚኒስቴር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ድንበር ማሻገርን መከላከል የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ሕጎችን አውጥተው ወደ ተግባር መግባታቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡፡ በሰመራ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነትና ከፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የተሰናዳው አህጉር አቀፍ ሲምፖዚየም ከትናንት ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል። ሲምፖዚየሙ "ሕገ-ወጥ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር፤ የሕግ፣ ማኅበራዊ እና ተቋማዊ አመለካከቶች" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ ነው።
ፖለቲካ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ የተያዘው ዕቅድ በስኬት የተፈፀመበት ነው -አቶ አደም ፋራህ
Jun 7, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገራዊ ግቦቹን እንዲያሳካ እና ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ በብልጽግና ፓርቲ የተያዘው ዕቅድ እና የተከናወኑ ዐበይት ተግባራት በስኬት የተፈፀሙበት መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። አቶ አደም ፋራህ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ላለፉት ሁለት ቀናት በሶማሌ ክልል ሸቤለይ ሪዞርት ከፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር እስከ ምርጫው ዕለት ያለውን የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ሥራዎች ዕቅድ አፈፃፀም በጥልቀት በመገምገም እና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ላይ በመግባባት መድረኩ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ለምርጫው ስኬታማነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፌዴራል እና የክልል ፀጥታ ኃይሎች፣ በታዛቢነት የተሳተፉ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ ተቋማት እንዲሁም ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በማሳየት ከለሊቱ 10 ሰዓት እስከ ሚቀጥለው ለሊት 10 ሰዓት ድምፅ ለመስጠት የተሰለፈው እና ለምርጫው ስኬት የሚችለውን ሁሉ ላደረገው ለተከበረው ሕዝብ፣ እንዲሁም ሌሎች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ ምስጋናችንን አቅርበዋል። ከግምገማዊ ውይይት መድረኩ ጎን ለጎን፣ የስብሰባው ተሳታፊ ከፍተኛ አመራሮች በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ በጅግጅጋ እየተከናወኑ ያሉ ዐበይት የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም በክልሉ መንግሥት እና በሕዝቡ ጥረት እየተመዘገቡ ያሉ አንጸባራቂ ስኬቶችን በተጨባጭ መመልከታቸውን ነው የገለጹት። የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራዎች የከተማዋን ገጽታ ሙሉ በሙሉ የቀየሩ፣ የተቀናጁ መሠረተ ልማቶችን ያሟሉ እና ፈጣን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን የፈጠሩ ናቸው ብለዋል አቶ አደም። ይህ ሥራ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን እና ከተማዋን የቀጣናው የልማት እና የንግድ ማዕከል እንድትሆን እንዳደረጋትም ጠቁመዋል። በክልሉ መንግሥት ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃውን አዲስ የፖሊስ ሆስፒታል ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሚሰጠው አገልግሎት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በተለይም የፖሊስ አባላት እና ቤተሰቦቻቸው የሚያገኙትን የጤና አገልግሎት በማላቅ፣ የፀጥታ ኃይሎች ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን በላቀ ሞራል እና ቁርጠኝነት እንዲወጡ የሚያግዝ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ነው ያሉት። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ትኩረት የሕዝብን አገልጋይነት ማረጋገጥ እና የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን ነው ያሉት አቶ አደም ፋራህ፣ በመላው ኢትዮጵያ የተገነቡት እና ግንባታቸው እየተጠናቀቀ ያሉት የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት የቢሮክራሲ ማነቆዎችን በመቅረፍ የዜጎችን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ እያሳደጉ እንደሚገኙም ገልጸዋል። በአጠቃላይ በጅግጅጋ የተመለከቱት ፈጣን እና ሁለንተናዊ ለውጦች የብልጽግና ፓርቲን የልማት እና የመልካም አስተዳደር እሳቤዎች እንዲሁም ፖሊሲዎች ውጤታማነት በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውን አስምረውበታል። ከተማዋ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገች ያለችበት አግባብ እጅግ የሚያስደስት፣ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ ምሥል ያየንበት እና ለሌሎች አካባቢዎችም አርአያ የሚሆን ነው ሲሉም ገልጸዋል። በከፍተኛ ትጋት እና ቁርጠኝነት እውነተኛ ዴሞክራሲን ከተጨባጭ የልማት፣ የመልካም አስተዳደር እና የሰላም ስኬቶች ጋር በማጣመር፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና በተግባር የማረጋገጥ ስኬታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር አሳይተዋል
Jun 7, 2026 126
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየታቸውን የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎችም እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ መካሄዱ ይታወቃል። ኢትዮጵያዊያን በመረጡበትና ኢትዮጵያም ባሸነፈችበት ምርጫ የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ አስተምህሮና ታዛቢነት የነቃ ተሳትፎ አድርገዋል። የምርጫ ሂደቱን በማስመልከትም የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌደሬሽንና የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር የሥራ ኃላፊዎች ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አሕመድ ሁሴን እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈጸም አቅም በተግባር የታየበት ነው። በምርጫውም በምርጫ አስተምህሮና ታዛቢነት በርካታ አባላትን በማሰማራት የሂደቱን ዴሞክራሲያዊነትና አሳታፊነት ማረጋገጥ የሚያስችል ተሳትፎ ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያንና የፖለቲካ ፓርቲዎች ነጻ፣ ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና በሁሉም መለኪያ የነቃ ተሳትፎ ያደረጉበት መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ተናግረዋል። ይህም ኢትዮጵያዊያንና የፖለቲካ ፓርቲዎች ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ መሰረት በመጣል ቁርጠኝነታቸውን በተግባር ያሳዩበት መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር መስዑድ ገበየሁ በበኩላቸው፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሰከነ ተሳትፎ የታየበትና ሰብዓዊ መብቶችን ያከበረ ነበር ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሃሳባቸውን ለህዝብ ባቀረቡበት ወቅት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጨምሮ በብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ የነበራቸው ትብብር አስደማሚ እንደነበር መታዘባቸውን ገልጸዋል። በምርጫ ወቅት በነበረው ትዝብትም ምርጫ ጣቢያዎች ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መራጮች ምቹና ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በተሟላ ሁኔታ የተጠቀሙበት ሁኔታን ፈጥሮ እንዳለፈ ገልጸዋል። በተጨማሪም የዘንድሮው የምርጫ ሂደት ከሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አንጻር በጥሩ ደረጃ ላይ የተከናወነና ስኬታማ እንደነበር አስታውቀዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ወጣቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር በመጠቀም የነቃ ተሳትፎ አድርገዋል ያለው ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ተወካይ አሌክሳንደር ንጉሴ ነው። በምርጫ ሂደቱ የነበረው የወጣቶችና የፖለቲካ ፓርቲዎች የነቃ ተሳትፎም ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጿል። በሂደቱ የፌዴሬሽኑ ታዛቢዎች ከተለያዩ የፖለቲካ ፖርቲዎች ተወካዮች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ከምርጫ አስፈፃሚዎች ጋር በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን በብቃት እንደተወጡ ተናግሯል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት እናታለም እንዳለ በበኩላቸው፤ በምርጫው ሂደት ሴቶች የነበራቸው ንቁ ተሳትፎ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝት በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። በሂደቱም በርካታ ሴቶች በምርጫ ታዛቢነትና በመራጭነት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብታቸውን በተግባር እንዲጠቀሙ ማድረግ እንደተቻለ አስረድተዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰብዓዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ በስኬት የተካሄደና የሰከነ የፖለቲካ ፉክክር የታየበት ነው
Jun 7, 2026 236
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰብዓዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ በስኬት የተካሄደና የሰከነ የፖለቲካ ፉክክር የታየበት መሆኑን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ገለጸ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ ውሎ፤ የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎች እስከ ዕኩለ ለሊት ድረስ ተካሂዶ ፍፃሜውን አግኝቷል። በዚህም ኢትዮጵያዊያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያም አሸንፋለች። ይህን ተከትሎም በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ስር የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶችን ይፋ እያደረጉ ሲሆን፤ ዜጎችም ጊዜያዊ ውጤቶችን እየተመለከቱ እንደሚገኙ ቦርዱ አስታውቋል። በምርጫ ሂደቱም በርካታ የሀገር ውስጥ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ አስተምህሮና ታዛቢነት፣ የኢጋድና የአፍሪካ ህብረት ልዑካን ደግሞ በምርጫ ታዛቢነት ስኬታማ ተሳትፎ አድርገዋል። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር መስዑድ ገበየሁ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዘንድሮው ምርጫ ዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ቆርጠኝነታቸውን አሳይተዋል። በምርጫ ፉክክር ሂደቱም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሲያቀርቡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ የነበራቸው ስልታዊ ትብብር አስደማሚ እንደነበር መታዘባቸውን ገልጸዋል። ይህም ፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጨምሮ ለሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅሞች መከበር የሰከነ የፖለቲካ ምኅዳር በመፍጠር እየተሳተፉ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ተናግረዋል። በምርጫ ወቅት በነበረው ትዝብትም ምርጫ ጣቢያዎች ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መራጮች ምቹና ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በተሟላ ሁኔታ የተጠቀሙበት መሆኑን አንስተዋል። በተለይም ምርጫ ጣቢያዎች ለአካል ጉዳተኞች፣ መስማት ለተሳናቸው፣ ነፍሰ ጡሮችና ጨቅላ ሕፃናት ለያዙ ወላጆች የተፈጠረው አስቻይ ምኅዳር ለመራጮች ምቹ ሁኔታን ፈጥሮ እንዳለፈ ገልጸዋል። በሌላ መልኩም የዘንድሮው የምርጫ ሂደት ከሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አንጻር በጥሩ ደረጃ ላይ የተከናወነና ስኬታማ እንደነበር አስታውቀዋል።
የሀገርን ሉዓላዊነት ለመጠበቅና ለማስከበር የትኛውንም መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን-ተመራቂ ወታደራዊ መኮንኖች
Jun 7, 2026 219
ድሬደዋ፣ግንቦት 30/2018(ኢዜአ)፦በትምህርት ቆይታቸው በቀሰሙት ዘመናዊ ወታደራዊ ሙያና ጥበብ በመታገዝ፣የሀገርን ሉዓላዊነትን ለማስከበር የትኛውንም ዓይነት መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ከሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ተመራቂ ወታደራዊ መኮንኖች ተናገሩ። የሁርሶ ዕጩ መኮንኖች ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ያሰለጠናቸውን የ27ኛ ዙር ፅናት ኮርስ ዕጩ መኮንኖች በትናንትናው እለት አስመርቋል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ በትምህርት ቆይታቸው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ዕጩ መኮንኖች ማዕረግ አልብሰዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል ምክትል መቶ አለቃ ዘካሪያስ አባተ እንደገለጹት፤ በትምህርት ቤቱ ያገኙትን ዘመናዊ ሥልጠናና የዳበረ ልምድ በመጠቀም፣ከሠራዊቱ ጎን በመሰለፍ የተጣለባቸውን ማንኛውንም ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ ናቸው። በኢትዮጵያ ዳር ድንበር ላይ በመሰማራት የሀገርንና የዜጎችን ጥቅም አስከብረው ማገልገላቸው፣ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃት የመፈጸም ትልቅ ልምድ እንዳስገኘላቸው የገለጹት ደግሞ ሌላው ተመራቂ መኮንን ምክትል መቶ አለቃ ታደለ ናኒዮ ናቸው። በማሰልጠኛ ቆይታቸው የተሰጣቸው ወታደራዊ የተግባርና የንድፈ-ሐሳብ ሥልጠና፤ ወደፊት የሚጠብቋቸውን ቀጣይ ተልዕኮዎች በላቀ ብቃትና ጀግንነት ለመወጣት ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ምክትል መቶ አለቃ ማስተዋል በለጠ በበኩላቸው፥ ሴት የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በማናቸውም ፈተና ውስጥ ሆነው በታላቅ ጀግንነትና ብቃት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር፣እንዲሁም የዜጎችን ደኅንነትና ከፍታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል መቶ አለቃ ሄዋን አማንም፤ ወደ አመራርነት መሻገር ትልቅ ሀገራዊና የሕዝብ ኃላፊነት መሸከም መሆኑን አስታውሰዋል። ሀገራቸውን ከውጭና ከውስጥ ጠላቶች ለመጠበቅ እንዲሁም የኢትዮጵያንና የሕዝቧን ከፍታ በፅናት ለማረጋገጥ የትኛውንም መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውንም አስምረውበታል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በንቃት የተሳተፉበት ምርጫ ነው
Jun 7, 2026 301
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በንቃት የተሳተፉበት ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንደነበር የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት እናታለም እንዳለ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሄደችውን ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኢጋድና የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ተከታትለውታል፡፡ ምርጫውን ከታዘቡት 55 የሀገር ውስጥ ሲቪክ ማህበራት መካከል አንዱ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ነው፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት እናታለም እንዳለ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ምርጫ ዜጎች መብታቸውን ተጠቅመው የሚበጃቸውን ፓርቲ የሚመርጡበት የዴሞክራሲ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ የሁሉም ማህበረሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን በመግለጽ፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶች ንቁ ተሳትፎ የተረጋገጠበት የፖለቲካ አውድ ነበር ብለዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ በመውሰድ ሴቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በጠቅላላ ምርጫው ንቁ ተሳታፊ የሚሆኑበትን የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠታቸውን ገልጸዋል፡፡ ከሁለት ሺህ በላይ አባላትን በማሰልጠን በዕለቱ የምርጫ ታዛቢዎችን መመደባቸውን ገልጸው፤ በርካታ ዜጎች የመራጭነት ካርድ በመውሰው ድምጽ ሰጥተዋል ብለዋል፡፡ ዜጎችን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሰላማዊ፣ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ድምፅ መስጠታቸውን በማንሳት፤የህዝቡን ተነሳሽነትና ፍላጎትም አድንቀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር በ1990 ዓ.ም የተቋቋመ ሲሆን ከግማሽ ሚሊዮን በላይ አባላት አሉት ተብሏል፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በጅግጅጋ ከተማ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል
Jun 6, 2026 1490
ጅግጅጋ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ እና የክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ከንቲባዎች ተሳትፈዋል። በጉብኝቱም የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማትን፣ የሶማሌ ክልል ፖሊስ ሆስፒታል ግንባታ ሂደትን፣ ሰይድ መሀመድ አብዲሌ ሀሰን መታሰቢያ ፓርክ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ያካተተ ነው። የክልሉ ፖሊስ ሆስፒታል ግንባታን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል። የኮሪደር ልማት ሥራውም የከተማዋን ገጽታ ለመቀየርና የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑ ተመልክቷል። ከዚህም ባለፈ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና የተቀናጀ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሕንፃ ግንባታ ክልሉ መልካም የልማት እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን ያመላክታል ተብሏል።
825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አድርገዋል
Jun 6, 2026 1497
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን 825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎ በስኬት መጠናቀቁን አስታውሰዋል። በምርጫው ዕለት ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ተጀምሮ የነበረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት፣ እስከ ምሽቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ ተራዝሞ መጠናቀቁ ይታወቃል። ከምርጫው ማግስት ጀምሮ ጊዜያዊ ውጤቶች በየምርጫ ጣቢያዎቹ ሲለጠፉ መቆየታቸውን የገለጹት ሰብሳቢዋ፤ የየጣቢያዎቹ ውጤቶች ምስጢራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ወደ የምርጫ ክልሎቹ እንዲደርሱ መደረጉንና የማዳመር ሥራው ሲከናወን መቆየቱን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ቦርዱ ምርጫ ባካሄደባቸው አጠቃላይ 1 ሺህ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል፣ 825ቱ የማዳመር ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው ጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርገዋል ብለዋል። የማዳመር ስራን በመስራት ላይ ያሉ ቀሪ የምርጫ ክልሎች መኖራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ እነዚህ ቀሪ የምርጫ ክልሎች ሂደቱን በጥቂት ቀናት ውስጥ አጠናቀው ውጤት ይፋ እንደሚያደርጉ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ አረጋግጠዋል። የምርጫ ሂደትን በሚመለከት ከፖለቲካ ፓርቲዎች የሚነሱ ቅሬታዎችን በሕጋዊ መንገድና በአግባቡ መፍታት የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋቱንም አስታውቀዋል። ይህንን የቅሬታ አፈታት ሂደት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግም ቦርዱ የሕግ ባለሙያዎችን መቅጠሩንና ጉዳዮችን በጥልቀት የሚመረምር ራሱን የቻለ የሕግ ባለሙያዎች ጉባኤ ማቋቋሙን ገልጸዋል። በዚሁ መሠረት እስካሁን 47 ያህል ቅሬታዎችን ተቀብሎ እያጣራ መሆኑንና የማጣራቱ ስራ እንደተጠናቀቀ የመጨረሻው ውጤት እንደሚያሳውቅ አረጋግጠዋል።
ብልፅግና ፓርቲ የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀመረ
Jun 6, 2026 1130
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም በጅግጅጋ ከተማ መገምገም ጀምሯል። መድረኩ የብልፅግና ፓርቲ የብሔራዊ የምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፓርቲው የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫና በምርጫው ወቅት የነበረውን አፈጻጸም ይገመግማል፣ ጠንካራና ደካማ አፈጻጸሞችን ይለያል፣ በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ፖለቲካ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ የተያዘው ዕቅድ በስኬት የተፈፀመበት ነው -አቶ አደም ፋራህ
Jun 7, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገራዊ ግቦቹን እንዲያሳካ እና ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ በብልጽግና ፓርቲ የተያዘው ዕቅድ እና የተከናወኑ ዐበይት ተግባራት በስኬት የተፈፀሙበት መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። አቶ አደም ፋራህ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ላለፉት ሁለት ቀናት በሶማሌ ክልል ሸቤለይ ሪዞርት ከፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር እስከ ምርጫው ዕለት ያለውን የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ሥራዎች ዕቅድ አፈፃፀም በጥልቀት በመገምገም እና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ላይ በመግባባት መድረኩ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ለምርጫው ስኬታማነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፌዴራል እና የክልል ፀጥታ ኃይሎች፣ በታዛቢነት የተሳተፉ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ ተቋማት እንዲሁም ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በማሳየት ከለሊቱ 10 ሰዓት እስከ ሚቀጥለው ለሊት 10 ሰዓት ድምፅ ለመስጠት የተሰለፈው እና ለምርጫው ስኬት የሚችለውን ሁሉ ላደረገው ለተከበረው ሕዝብ፣ እንዲሁም ሌሎች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ ምስጋናችንን አቅርበዋል። ከግምገማዊ ውይይት መድረኩ ጎን ለጎን፣ የስብሰባው ተሳታፊ ከፍተኛ አመራሮች በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ በጅግጅጋ እየተከናወኑ ያሉ ዐበይት የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም በክልሉ መንግሥት እና በሕዝቡ ጥረት እየተመዘገቡ ያሉ አንጸባራቂ ስኬቶችን በተጨባጭ መመልከታቸውን ነው የገለጹት። የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራዎች የከተማዋን ገጽታ ሙሉ በሙሉ የቀየሩ፣ የተቀናጁ መሠረተ ልማቶችን ያሟሉ እና ፈጣን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን የፈጠሩ ናቸው ብለዋል አቶ አደም። ይህ ሥራ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን እና ከተማዋን የቀጣናው የልማት እና የንግድ ማዕከል እንድትሆን እንዳደረጋትም ጠቁመዋል። በክልሉ መንግሥት ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃውን አዲስ የፖሊስ ሆስፒታል ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሚሰጠው አገልግሎት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በተለይም የፖሊስ አባላት እና ቤተሰቦቻቸው የሚያገኙትን የጤና አገልግሎት በማላቅ፣ የፀጥታ ኃይሎች ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን በላቀ ሞራል እና ቁርጠኝነት እንዲወጡ የሚያግዝ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ነው ያሉት። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ትኩረት የሕዝብን አገልጋይነት ማረጋገጥ እና የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን ነው ያሉት አቶ አደም ፋራህ፣ በመላው ኢትዮጵያ የተገነቡት እና ግንባታቸው እየተጠናቀቀ ያሉት የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት የቢሮክራሲ ማነቆዎችን በመቅረፍ የዜጎችን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ እያሳደጉ እንደሚገኙም ገልጸዋል። በአጠቃላይ በጅግጅጋ የተመለከቱት ፈጣን እና ሁለንተናዊ ለውጦች የብልጽግና ፓርቲን የልማት እና የመልካም አስተዳደር እሳቤዎች እንዲሁም ፖሊሲዎች ውጤታማነት በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውን አስምረውበታል። ከተማዋ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገች ያለችበት አግባብ እጅግ የሚያስደስት፣ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ ምሥል ያየንበት እና ለሌሎች አካባቢዎችም አርአያ የሚሆን ነው ሲሉም ገልጸዋል። በከፍተኛ ትጋት እና ቁርጠኝነት እውነተኛ ዴሞክራሲን ከተጨባጭ የልማት፣ የመልካም አስተዳደር እና የሰላም ስኬቶች ጋር በማጣመር፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና በተግባር የማረጋገጥ ስኬታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር አሳይተዋል
Jun 7, 2026 126
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያን ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየታቸውን የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎችም እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ መካሄዱ ይታወቃል። ኢትዮጵያዊያን በመረጡበትና ኢትዮጵያም ባሸነፈችበት ምርጫ የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ አስተምህሮና ታዛቢነት የነቃ ተሳትፎ አድርገዋል። የምርጫ ሂደቱን በማስመልከትም የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌደሬሽንና የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር የሥራ ኃላፊዎች ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አሕመድ ሁሴን እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈጸም አቅም በተግባር የታየበት ነው። በምርጫውም በምርጫ አስተምህሮና ታዛቢነት በርካታ አባላትን በማሰማራት የሂደቱን ዴሞክራሲያዊነትና አሳታፊነት ማረጋገጥ የሚያስችል ተሳትፎ ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያዊያንና የፖለቲካ ፓርቲዎች ነጻ፣ ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና በሁሉም መለኪያ የነቃ ተሳትፎ ያደረጉበት መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ተናግረዋል። ይህም ኢትዮጵያዊያንና የፖለቲካ ፓርቲዎች ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ መሰረት በመጣል ቁርጠኝነታቸውን በተግባር ያሳዩበት መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር መስዑድ ገበየሁ በበኩላቸው፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሰከነ ተሳትፎ የታየበትና ሰብዓዊ መብቶችን ያከበረ ነበር ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሃሳባቸውን ለህዝብ ባቀረቡበት ወቅት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጨምሮ በብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ የነበራቸው ትብብር አስደማሚ እንደነበር መታዘባቸውን ገልጸዋል። በምርጫ ወቅት በነበረው ትዝብትም ምርጫ ጣቢያዎች ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መራጮች ምቹና ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በተሟላ ሁኔታ የተጠቀሙበት ሁኔታን ፈጥሮ እንዳለፈ ገልጸዋል። በተጨማሪም የዘንድሮው የምርጫ ሂደት ከሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አንጻር በጥሩ ደረጃ ላይ የተከናወነና ስኬታማ እንደነበር አስታውቀዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ወጣቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር በመጠቀም የነቃ ተሳትፎ አድርገዋል ያለው ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ተወካይ አሌክሳንደር ንጉሴ ነው። በምርጫ ሂደቱ የነበረው የወጣቶችና የፖለቲካ ፓርቲዎች የነቃ ተሳትፎም ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጿል። በሂደቱ የፌዴሬሽኑ ታዛቢዎች ከተለያዩ የፖለቲካ ፖርቲዎች ተወካዮች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ከምርጫ አስፈፃሚዎች ጋር በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን በብቃት እንደተወጡ ተናግሯል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት እናታለም እንዳለ በበኩላቸው፤ በምርጫው ሂደት ሴቶች የነበራቸው ንቁ ተሳትፎ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝት በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። በሂደቱም በርካታ ሴቶች በምርጫ ታዛቢነትና በመራጭነት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብታቸውን በተግባር እንዲጠቀሙ ማድረግ እንደተቻለ አስረድተዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰብዓዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ በስኬት የተካሄደና የሰከነ የፖለቲካ ፉክክር የታየበት ነው
Jun 7, 2026 236
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰብዓዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ በስኬት የተካሄደና የሰከነ የፖለቲካ ፉክክር የታየበት መሆኑን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ገለጸ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ ውሎ፤ የድምፅ አሰጣጥ ባልተጠናቀቀባቸው ጣቢያዎች እስከ ዕኩለ ለሊት ድረስ ተካሂዶ ፍፃሜውን አግኝቷል። በዚህም ኢትዮጵያዊያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያም አሸንፋለች። ይህን ተከትሎም በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ስር የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶችን ይፋ እያደረጉ ሲሆን፤ ዜጎችም ጊዜያዊ ውጤቶችን እየተመለከቱ እንደሚገኙ ቦርዱ አስታውቋል። በምርጫ ሂደቱም በርካታ የሀገር ውስጥ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ አስተምህሮና ታዛቢነት፣ የኢጋድና የአፍሪካ ህብረት ልዑካን ደግሞ በምርጫ ታዛቢነት ስኬታማ ተሳትፎ አድርገዋል። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት ዳይሬክተር መስዑድ ገበየሁ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዘንድሮው ምርጫ ዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ቆርጠኝነታቸውን አሳይተዋል። በምርጫ ፉክክር ሂደቱም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሲያቀርቡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ የነበራቸው ስልታዊ ትብብር አስደማሚ እንደነበር መታዘባቸውን ገልጸዋል። ይህም ፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጨምሮ ለሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅሞች መከበር የሰከነ የፖለቲካ ምኅዳር በመፍጠር እየተሳተፉ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ተናግረዋል። በምርጫ ወቅት በነበረው ትዝብትም ምርጫ ጣቢያዎች ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መራጮች ምቹና ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በተሟላ ሁኔታ የተጠቀሙበት መሆኑን አንስተዋል። በተለይም ምርጫ ጣቢያዎች ለአካል ጉዳተኞች፣ መስማት ለተሳናቸው፣ ነፍሰ ጡሮችና ጨቅላ ሕፃናት ለያዙ ወላጆች የተፈጠረው አስቻይ ምኅዳር ለመራጮች ምቹ ሁኔታን ፈጥሮ እንዳለፈ ገልጸዋል። በሌላ መልኩም የዘንድሮው የምርጫ ሂደት ከሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አንጻር በጥሩ ደረጃ ላይ የተከናወነና ስኬታማ እንደነበር አስታውቀዋል።
የሀገርን ሉዓላዊነት ለመጠበቅና ለማስከበር የትኛውንም መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን-ተመራቂ ወታደራዊ መኮንኖች
Jun 7, 2026 219
ድሬደዋ፣ግንቦት 30/2018(ኢዜአ)፦በትምህርት ቆይታቸው በቀሰሙት ዘመናዊ ወታደራዊ ሙያና ጥበብ በመታገዝ፣የሀገርን ሉዓላዊነትን ለማስከበር የትኛውንም ዓይነት መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ከሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ተመራቂ ወታደራዊ መኮንኖች ተናገሩ። የሁርሶ ዕጩ መኮንኖች ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ያሰለጠናቸውን የ27ኛ ዙር ፅናት ኮርስ ዕጩ መኮንኖች በትናንትናው እለት አስመርቋል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ በትምህርት ቆይታቸው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ዕጩ መኮንኖች ማዕረግ አልብሰዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል ምክትል መቶ አለቃ ዘካሪያስ አባተ እንደገለጹት፤ በትምህርት ቤቱ ያገኙትን ዘመናዊ ሥልጠናና የዳበረ ልምድ በመጠቀም፣ከሠራዊቱ ጎን በመሰለፍ የተጣለባቸውን ማንኛውንም ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ ናቸው። በኢትዮጵያ ዳር ድንበር ላይ በመሰማራት የሀገርንና የዜጎችን ጥቅም አስከብረው ማገልገላቸው፣ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃት የመፈጸም ትልቅ ልምድ እንዳስገኘላቸው የገለጹት ደግሞ ሌላው ተመራቂ መኮንን ምክትል መቶ አለቃ ታደለ ናኒዮ ናቸው። በማሰልጠኛ ቆይታቸው የተሰጣቸው ወታደራዊ የተግባርና የንድፈ-ሐሳብ ሥልጠና፤ ወደፊት የሚጠብቋቸውን ቀጣይ ተልዕኮዎች በላቀ ብቃትና ጀግንነት ለመወጣት ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ምክትል መቶ አለቃ ማስተዋል በለጠ በበኩላቸው፥ ሴት የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በማናቸውም ፈተና ውስጥ ሆነው በታላቅ ጀግንነትና ብቃት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር፣እንዲሁም የዜጎችን ደኅንነትና ከፍታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል መቶ አለቃ ሄዋን አማንም፤ ወደ አመራርነት መሻገር ትልቅ ሀገራዊና የሕዝብ ኃላፊነት መሸከም መሆኑን አስታውሰዋል። ሀገራቸውን ከውጭና ከውስጥ ጠላቶች ለመጠበቅ እንዲሁም የኢትዮጵያንና የሕዝቧን ከፍታ በፅናት ለማረጋገጥ የትኛውንም መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውንም አስምረውበታል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በንቃት የተሳተፉበት ምርጫ ነው
Jun 7, 2026 301
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በንቃት የተሳተፉበት ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንደነበር የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት እናታለም እንዳለ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሄደችውን ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኢጋድና የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ተከታትለውታል፡፡ ምርጫውን ከታዘቡት 55 የሀገር ውስጥ ሲቪክ ማህበራት መካከል አንዱ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ነው፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት እናታለም እንዳለ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ምርጫ ዜጎች መብታቸውን ተጠቅመው የሚበጃቸውን ፓርቲ የሚመርጡበት የዴሞክራሲ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ የሁሉም ማህበረሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን በመግለጽ፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶች ንቁ ተሳትፎ የተረጋገጠበት የፖለቲካ አውድ ነበር ብለዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ በመውሰድ ሴቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በጠቅላላ ምርጫው ንቁ ተሳታፊ የሚሆኑበትን የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠታቸውን ገልጸዋል፡፡ ከሁለት ሺህ በላይ አባላትን በማሰልጠን በዕለቱ የምርጫ ታዛቢዎችን መመደባቸውን ገልጸው፤ በርካታ ዜጎች የመራጭነት ካርድ በመውሰው ድምጽ ሰጥተዋል ብለዋል፡፡ ዜጎችን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሰላማዊ፣ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ድምፅ መስጠታቸውን በማንሳት፤የህዝቡን ተነሳሽነትና ፍላጎትም አድንቀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር በ1990 ዓ.ም የተቋቋመ ሲሆን ከግማሽ ሚሊዮን በላይ አባላት አሉት ተብሏል፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በጅግጅጋ ከተማ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል
Jun 6, 2026 1490
ጅግጅጋ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ እና የክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ከንቲባዎች ተሳትፈዋል። በጉብኝቱም የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማትን፣ የሶማሌ ክልል ፖሊስ ሆስፒታል ግንባታ ሂደትን፣ ሰይድ መሀመድ አብዲሌ ሀሰን መታሰቢያ ፓርክ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ያካተተ ነው። የክልሉ ፖሊስ ሆስፒታል ግንባታን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል። የኮሪደር ልማት ሥራውም የከተማዋን ገጽታ ለመቀየርና የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑ ተመልክቷል። ከዚህም ባለፈ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና የተቀናጀ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሕንፃ ግንባታ ክልሉ መልካም የልማት እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን ያመላክታል ተብሏል።
825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አድርገዋል
Jun 6, 2026 1497
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን 825 የምርጫ ክልሎች ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎ በስኬት መጠናቀቁን አስታውሰዋል። በምርጫው ዕለት ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ተጀምሮ የነበረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት፣ እስከ ምሽቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ ተራዝሞ መጠናቀቁ ይታወቃል። ከምርጫው ማግስት ጀምሮ ጊዜያዊ ውጤቶች በየምርጫ ጣቢያዎቹ ሲለጠፉ መቆየታቸውን የገለጹት ሰብሳቢዋ፤ የየጣቢያዎቹ ውጤቶች ምስጢራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ወደ የምርጫ ክልሎቹ እንዲደርሱ መደረጉንና የማዳመር ሥራው ሲከናወን መቆየቱን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ቦርዱ ምርጫ ባካሄደባቸው አጠቃላይ 1 ሺህ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል፣ 825ቱ የማዳመር ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው ጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርገዋል ብለዋል። የማዳመር ስራን በመስራት ላይ ያሉ ቀሪ የምርጫ ክልሎች መኖራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ እነዚህ ቀሪ የምርጫ ክልሎች ሂደቱን በጥቂት ቀናት ውስጥ አጠናቀው ውጤት ይፋ እንደሚያደርጉ የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ አረጋግጠዋል። የምርጫ ሂደትን በሚመለከት ከፖለቲካ ፓርቲዎች የሚነሱ ቅሬታዎችን በሕጋዊ መንገድና በአግባቡ መፍታት የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋቱንም አስታውቀዋል። ይህንን የቅሬታ አፈታት ሂደት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግም ቦርዱ የሕግ ባለሙያዎችን መቅጠሩንና ጉዳዮችን በጥልቀት የሚመረምር ራሱን የቻለ የሕግ ባለሙያዎች ጉባኤ ማቋቋሙን ገልጸዋል። በዚሁ መሠረት እስካሁን 47 ያህል ቅሬታዎችን ተቀብሎ እያጣራ መሆኑንና የማጣራቱ ስራ እንደተጠናቀቀ የመጨረሻው ውጤት እንደሚያሳውቅ አረጋግጠዋል።
ብልፅግና ፓርቲ የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀመረ
Jun 6, 2026 1130
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም በጅግጅጋ ከተማ መገምገም ጀምሯል። መድረኩ የብልፅግና ፓርቲ የብሔራዊ የምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፓርቲው የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫና በምርጫው ወቅት የነበረውን አፈጻጸም ይገመግማል፣ ጠንካራና ደካማ አፈጻጸሞችን ይለያል፣ በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ማህበራዊ
ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት የምርምርና የማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jun 7, 2026 132
ሰመራ፣ግንቦት 30/2018(ኢዜአ):-ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የሚከናወኑ የምርምር ሥራዎችንና የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ገለጹ። ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ደግሞ በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ የሚገኝ አሳሳቢ ክስተት ነው። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መንግሥትና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ችግሩን ለመግታት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ። በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያላቸውን የምርምር አቅምና የማኅበረሰብ አገልግሎት ድርሻ በመጠቀም፣ የሕገ-ወጥ ዝውውርን መነሻ ምክንያቶች ለይቶ ማውጣትና ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ ላይ ሰፊ ኃላፊነት እንዳለባቸው ይታመናል። በዚሁ ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች እንደገለጹት፤ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የሚከናወኑ የምርምር ሥራዎችና የማኅበረሰብ አገልግሎቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የህግና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኀላፊ ቹዌል ኦኬደ እንዳሉት ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርና ፍልሰትን ከመከላከል አኳያ የተለያዩ ተግባራት በቅንጅት ተከናውነዋል። ስልጠናዎችን በማዘጋጀት በአካባቢው በሚገኙ አምስት ቋንቋዎች ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ለአብነት አንስተዋል። የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ኃላፊ አቶ አብርሃም ክንፈ፤ ዩኒቨርሲቲው ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመከላከል ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎት መስጠቱን አስታውቀዋል። ማዕከላቱ በተለያዩ አካባቢዎች የሕግ ቢሮዎችን በመክፈት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን እንደሚሰጡ ገልጸዋል። በተጨማሪም ተጎጂዎች የሕግ ውክልና እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ፣ የሰብአዊ መብት አያያዝን የተመለከቱ ተግባራትን የማስተባበር ሥራ እንደሚያከናውኑ ተናግረዋል። የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የህግና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኀላፊ ሳለአምላክ አታላይ እንዳሉት ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል በክልሉ ከሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው። የምርምርና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በማዘጋጀትና የህግ ድጋፍ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። መንግሥት መደበኛ ያልሆነ የዜጎችን ፍልሰትና ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በማስቀረት፣ ዜጎች ሕጋዊ አሠራርን ተከትለው መሥራት የሚችሉበትን ዕድል እያመቻቸ እንደሚገኝ የገለጹት ደግሞ የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዘካሪያስ ኤርኮላ(ዶ/ር) ናቸው። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት የሚመራበትን ሕግ እንዲሁም የፍትሕ ሚኒስቴር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ድንበር ማሻገርን መከላከል የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ሕጎችን አውጥተው ወደ ተግባር መግባታቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡፡ በሰመራ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነትና ከፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የተሰናዳው አህጉር አቀፍ ሲምፖዚየም ከትናንት ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል። ሲምፖዚየሙ "ሕገ-ወጥ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር፤ የሕግ፣ ማኅበራዊ እና ተቋማዊ አመለካከቶች" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ ነው።
በምስራቅ ቦረና ዞን ከ16 ሺህ በላይ የወባ ትንኝ መከላከያ አጎበር ለነዋሪዎች ተሰራጨ
Jun 7, 2026 225
ነገሌ ቦረና፣ ግንቦት 30/2018 (ኢዜእ):-በምስራቅ ቦረና ዞን ቆላማ ወረዳዎች ከ16 ሺህ በላይ የወባ ትንኝ መከላከያ አጎበር መሰራጨቱን የዞኑ ጤና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ በጽህፈት ቤቱ የወባ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ አቶ ገዛሀኝ ኪታባ በዞኑ የወባ በሽታን ለመከላከል ለአካባቢ ንጽህናና ቁጥጥር ሥራዎች ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። በተለይ ህብረተሰቡን በዘመቻ በሚከናወኑ የአካባቢ ንጽህና ጥበቃ ሥራዎች ላይ የጤና ባለሙያዎችና ድጋፍ ሰጭ ሠራተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡ የግልና የአካባቢ ጥበቃ ሥራውን ለማሳካትም ለ67 ሺህ 381 ዜጎች የግንዛቤ ማሰጨበጫ ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል። ከዚህ ባለፈ የወባ ትንኝ መከላከያ አጎበር ስርጭት በዞኑ ጉሚ ኤልደሎ እና ሊበን ወረዳዎች ባሉ 11 የገጠር ቀበሌዎች መካሄዱን አቶ አቶ ገዛሀኝ አስታውቀዋል፡፡ የተሰራጨው አጎበርም 31ሺህ 639 የአርብቶ አደር ቤተሰብ አባላትን ከወባ በሽታ ለመከላከል የሚያስችል ነው ብለዋል። የአልጋ አጎበሩ በፌደራል መንግስት የቀረበ መሆኑን የገለጹት ባለሙያው፣ ከ9 ሚሊዮን 660 ሺህ ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ እንዳለውም ተናግረዋል፡፡ ከአጎበር ሥርጭቱ ጎን ለጎን ለወባ በሽታ መራቢያ ምቹ በሆነ 241 ሺህ 841 እስኩየር ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የጸረ ወባ መድሀኒት እርጭት መካሄዱን ገልጸዋል፡፡ በየዓመቱ በዞኑ የወባ በሽታ በሚቀሰቀስባቸው ዘጠኝ ወረዳዎች ውስጥ ባሉ 108 ቀበሌዎች ውሃ ባቆሩ አካባቢዎች የወባ መከላከያ ኬሚካል እርጭት መካሄዱንም ጠቁመዋል፡፡
በአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት አካል የሆኑ አዳዲስ የአስፋልት መንገዶች እየተገነቡ ነው
Jun 7, 2026 241
አሶሳ፤ ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፦ በአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት አካል የሆኑ አዳዲስ የአስፋልት መንገዶች እየተገነቡ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሙሐመድ አልማሂ ገለጹ። በዚህም መሠረት ከአሶሳ ሕዳሴ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ከተማዋ የሚያስገባው የአስፋልት መንገድ ግንባታ መጠናቀቁን ኃላፊው ለኢዜአ ተናግረዋል። እስከ 22 ሜትር ስፋት ያለው ይህ መንገድ 1 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር እንደሚረዝም ጠቁመው፤ የነበረውን የትራፊክ መጨናነቅ ከማስቀረቱም ባሻገር ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት እንደሆነ አስረድተዋል። በተያያዘም በከተማዋ በሌላኛው አቅጣጫ 4 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የአስፋልት መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑን አመላክተዋል። የአስፋልት መንገዶቹ ግንባታ በአዲስ መልክ ባለሁለት መስመር መንገድ ተደርጎ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። በሁለት አቅጣጫ እየተገነቡ የሚገኙት የአስፋልት መንገዶቹ የከተማዋን ዕድገት ታሳቢ ያደረጉ፣ የኮሪደር ልማትን ያካተቱ እና ምቹ የሥራ አካባቢን በመፍጠር የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል። በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የአስፋልት መንገዶችን በመጠገን ለአገልግሎት ክፍት የማድረጉ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አስታውቀዋል።
በጋምቤላ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሂደት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል
Jun 6, 2026 1037
ጋምቤላ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከአጋር አካላት ጋር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። በጋምቤላ ክልል ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በማስቀረት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን የሚገመግም መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሄዷል። የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አርያት ኡጁሉ በመድረኩ እንደገለጹት፤ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በማስቀረት የሴቶችን የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ያስፈልጋል። በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ያለእድሜ ጋብቻ፣ በጋብቻ ላይ ጋብቻና ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በሴቶች ላይ የሚያደርሱት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት ከጎጂ ልማድ ጋር ተያይዞ ሴቶች ላይ ይደርስ የነበረውን ችግር በማስቀረት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ለውጦች መምጣታቸውን ተናግረዋል። በተለይም ቢሮው ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት ሴቶችን በእርሻ ልማት፣ በእርባታና ሌሎች የገቢ ማስገኛ ስራዎች በማሰማራት በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ረገድ አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል። የተገኙትን ለውጦች ይበልጥ ለማጠናከር አሁንም የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በቢሮው ግንዛቤ ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ግሩም ገብረኢየሱስ እንዳሉት፤ በክልሉ በሁሉም ቀበሌዎች የጎጂ ልማዳዊ ድርጊት አስወጋጅ ኮሚቴ በማቋቋም ያለእድሜ ጋብቻን ጨምሮ ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቀረት በትኩረት እየተሰራ ነው። ቢሮው ከጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቀረት የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። መድረኩ ላይ የክልሉ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን፣ በተከናወኑት ስራዎች ዙሪያ ሪፖርቶች ቀርበው ተገምግመዋል። በውይይት መድረኩ መጨረሻ አቅም ለሌላቸው ሴቶች የእርባታ ፍየሎችና የገንዘብ ድጋፍ ለተወካዮቻቸው ተበርክቷል።
ኢኮኖሚ
የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን ለህብረተሰቡ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስችሏል
Jun 7, 2026 44
አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎች ገለጹ፡፡ መንግስት በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ እያደረጋቸው ያሉ ሁለንተናዊ ማሻሻያዎችና በመዲናዋ የተገነቡት ዘመናዊ የአውቶብስ ፌርማታዎች ለአገልግሎቱ መቀላጠፍና ለተሳፋሪዎች ምቾት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው፡፡ በመዲናዋ ደረጃቸውን በጠበቁና ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ለማህበረሰቡ የተሳለጠ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ገቢራዊ ተደርጓል፡፡ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ በሚገኙ ከተሞች ሳምንቱን ሙሉ ያለማቋረጥ የትራንስፖርት አገልግሎት በማቅረብ ላይ ያሉት የከተማ አውቶብሶች ለነዋሪዎች ኢኮኖሚዊና ማህበራዊ እፎይታን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑት አቶ መኮንን ለገሰ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የብዙሃን ትራንስፖርት ከሌሎች አማራጮች አንጻር አነስተኛ ታሪፍ ያለው በመሆኑ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ትልቅ አቅም ይፈጥራል፡፡ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳ የሚንቀሳቀሱ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይሄውም ያለ ምንም እንግልት በሰዓታቸው የሥራ ቦታቸው ላይ እንዲገኙ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡ ገቢያቸውን ያማከለና ተመጣጣኝ የትራንስፖርት አገልግሎት ከማግኘት ባለፈ ለሥራቸው መቃናትና ምርታማነት የጎላ አበርክቶ እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ መስከረም ዳመነ፤ አገልግሎቱ በየጊዜው እየተሻሻለ በመምጣቱ ጠዋትም ሆነ ማታ ፈጣን፣ ምቹና ቀልጣፋ ግልጋሎት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን የነዋሪዎች የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ በማሳለጥ ገንቢ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡ የከተማ አውቶብስ አሽከርካሪዎች በበኩላቸው ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገው አዲሱ አሠራር በሥራቸው ላይ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ አቶ ያለው ነጋ በትራንስፖርት ዘርፉ የተተገበረው ሪፎርም በካሜራና ጂፒኤስ (GPS) የታገዘ ዘመናዊ አሰራርን በማምጣት የአሽከርካሪዎችን የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደጉን ገልጸዋል፡፡ ቴክኖሎጂው ቀደም ሲል በፌርማታዎች ይስተዋሉ የነበሩትን ሰልፎች በማስቀረት በመዲናዋና ከዙሪያ ከተሞች ለሚመጡ ተጠቃሚዎች ተመራጭ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላኛዋ አሽከርካሪ ወይዘሮ ፍሬህይወት ኤካ፤ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን በተለይ ርቀት ላላቸው መስመሮች ከታሪፍ አንፃር እጅግ አዋጭ ነው ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን የሚተኩ እና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶች በስፋትና በጥራት እንዲመረቱ አስችሏል
Jun 7, 2026 161
ኮምቦልቻ ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ምርትን በመተካትና ለውጭ ምንዛሬ ግኝት የሚሆኑ ምርቶችን በጥራትና በስፋት በማምረት ረገድ ለዘርፉ እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለፁ። «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው የአማራ ክልል ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በኮምቦልቻ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንደገለጹት፤ ንቅናቄው ባለፉት ዓመታት የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማሳደግና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ከፍተኛ ሚና አበርክቷል። ሚኒስትሩ አክለውም፣ በንቅናቄው አማካኝነት ኢንዱስትሪዎችን መደገፍ፣ መሠረተ ልማቶችን ማሟላት፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና በተግዳሮቶች ላይ መፍትሔ መስጠት መቻሉን ገልጸው፤ በእነዚህም ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል። በተጨማሪም ንቅናቄው የገቢ ምርቶችን ከመተካትና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶችን በጥራትና በብዛት ከማምረት ባሻገር፣ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቻሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል። በአማራ ክልልም ንቅናቄው በርካታ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩና አዳዲስ ባለሃብቶችም በኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፤ በክልሉ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተቻለ ሲሆን፣ ይህም የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ንቅናቄው የገቢ ምርቶችን በመተካትና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረት ረገድ ካስገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር፣ ማኅበረሰቡ በሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀምና በራሱ ምርት የመኩራት ባሕል እንዲያዳብር ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ተናግረዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጣይም ዘርፉን የመደገፍ፣ የማዘመንና የማስፋት ሥራዎችን በማጠናከር ይበልጥ ተጠቃሚ ለመሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። አክለውም የክልሉ መንግሥት ለዚህ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ በበኩላቸው፤ በንቅናቄው አማካኝነት ባለፉት አራት ዓመታት 496 የሚሆኑ አዳዲስና ነባር ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፉ ከ125 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል። አቶ እንድሪስ አክለውም፤ በንቅናቄው አማካኝነት ከባለሀብቶች ጋር በቅርብ በመሥራት ምርቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የብድር አቅርቦት እንዲያገኙ፣ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉላቸው እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያገኙ መቻሉን ገልጸዋል። በመርሐግብሩ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
በክልሉ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በበጀት ዓመቱ 158 መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደማምረት ገብተዋል-ቢሮው
Jun 7, 2026 256
ኮምቦልቻ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በበጀት ዓመቱ 158 መካከለኛ እና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በአዲስ መልክ ማምረት መጀመራቸው ተገለጸ። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እንዲሁም ሌሎች የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሃግብር በኮምቦልቻ ከተማ እየተካሄደ ነው። የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተፈሪ ታረቀኝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የነበሩ ችግሮችን እየፈታ መጥቷል። በተለይም ባለሃብቱ ያነሳቸው የነበሩ የማስፋፊያና የአዳዲስ ኢንቨስትመንት ቦታዎች ጥያቄን፣ የብድርና የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ማስቻሉን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ይህም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ከማስፋፋት ባሻገር የማምረት አቅማቸውን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማስፋት እያገዘ መሆኑን ነው ያስረዱት። በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ወራት ብቻ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄው 158 መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በአዲስ መልክ ማምረት መጀመራቸውንም ተናግረዋል። የፌደራልና የክልሉ አመራሮቹ የተለያዩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በቀጣይም ከባለሀብቶች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ባለው በዚህ መርሃግብር ላይ 145 ኢንዱስትሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
የአረንጓዴ ዐሻራ እና የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብሮች ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምቹ ሁኔታ ፈጥረዋል
Jun 7, 2026 264
ጋምቤላ፤ ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአረንጓዴ ዐሻራ እና የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብሮች የፈጠሩትን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስኬታማ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጋምቤላ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ የተተገበሩት የአረንጓዴ አሻራ እና የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብሮች ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስኬታማነት ምቹ ሁኔታ ፈጥረዋል ጋምቤላ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የአረንጓዴ አሻራ እና የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብሮች የፈጠሩትን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ረገድ ስኬታማ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ የተሸረሸሩ መሬቶችን ለማገገም እና የደን ሽፋንን ለማሳደግ ታስቦ እየተካሄደ ያለ መጠነ-ሰፊ ንቅናቄ ነው። በሌላ በኩል፣ የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የሀገሪቱን የምግብና ሥነ-ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የእንስሳት፣ የዶሮ፣ የንብ፣ እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ምርታማነትን በየቤተሰቡ ደረጃ ለማሳደግ ያለመ ነው። እነዚህ ሁለቱ መርሃ-ግብሮች እርስ በርሳቸው የሚደጋገፉ በመሆናቸው፣ በአንድ በኩል አካባቢን ሲጠብቁ በሌላ በኩል ደግሞ ለተቀናጀ የግብርና ልማት መሳካት ትልቅ መሠረት ጥለዋል። በጋምቤላ ክልልም በሁለቱ መርሃግብሮች የተከናወኑት ተግባራት ውጤት እያስገኙ ነው። የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድሮው ቱት ለኢዜአ እንደገለጹት የአረንጓዴ አሸራና የሌማት ትሩፋት መርሃግብሮች የፈጠሯቸውን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም በክልሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስኬታማ ስራዎች እየተከናወኑ ነው። ቀደም ሲል ለፍጆታ ብቻ ይመረት የነበረው አትክልት አሁን ላይ ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ሐባብና ብርቱካንን ጨምሮ ሌሎች አትክልትና ፍራፍሬዎች በአርሶ አደሮችና በባለሃብቶች በስፋት እየተመረቱ ለገበያ እየቀረቡ ነው ብለዋል። በተለይም በማጃንግ ዞን በጎደሬና በመንጌሽ ወረዳዎች አቮካዶና ሙዝን ጨምሮ ሌሎች የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ወደ አዲስ አበባና ሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለገበያ በስፋት እየቀረቡ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በክልሉ በዘንድሮው ክረምትም ከአረንጓዴ አሻራ ልማቱ ጋር በማቀናጀት አቮካዶን ጨምሮ ከ8 ሚሊዮን በላይ የፍራፍሬና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል። በቢሮው የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም አስተባበሪ አቶ ሀብታሙ ገዳሙ እንዳሉት የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ መረሃ ግብር እንደ ሀገር የግብርናውን ዘርፍ ለማገዝ ከተቀረጹት ፕሮግራሞች መካከል አንዱ ነው። በፕሮግራሙ እየተሰሩ ከሚገኙት የእሴት ሰንሰለት ሰብሎች መካከል አቮካዶ፣ ስንዴ፣ በቆሎና ሌሎችም እንደሚገኙበት አስተባበሪው ገልጸዋል። በዘርፉ ልማት ከተሰማሩት አርሶ አደሮች መካከል የጎደሬ ወረዳ ጌለሻ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሉቃስ ጎርሾ በሰጡት አትያየት አካባቢው አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ለሁሉም የግብርና ልማት አመች ነው። እናም ሙዝ፣ አቮካዶና ሌሎችንም የሰብል እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬዎችን በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው በገበያ ትስስር በኩልም የመንግስት እገዛ እንሚሹ ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በሙዝ ልማት በስፋት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆኑን የገለጸው ደግሞ የዚሁ ቀበሌ ነዋር ወጣት ሮቤል ሮኬት ነው። በአሁኑ ወቅት ሰባት ሄክታር የሚደርስ ሙዝ በማልማት ምርቱን ወደ አዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች በመሸጥ ተጠቃሚ መሆኑን ጠቁመው የገበያ ትስስሩ ሊጠናከር ይገበል ብሏል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል
Jun 5, 2026 1056
ጎንደር፤ ግንቦት 28/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። በኢትዮጵያ በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በኢኖቬሽን ዘርፍ የተቀረፁ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መተግበር የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዳዲስ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ለማበረታታት ያቋቋመው የቢዝነስና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ማእከል በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተመርቆ ስራ ጀምሯል። ዩኒቨርሲቲው የማእከሉን ተልአኮና አላማ ማሳካት እንዲቻል ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የስምምነት ፊርማም ዛሬ አከናውኗል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዲጂታላይዜሽን የሚመራ ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ብለዋል። ኢኖቬሽንን ከማበረታታትና ከመደገፍ አንጻር ለፈጠራ ሃሳቦችና ስታርታፖች ምቹ ምህዳር ለመፍጠር ከምርምርና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቁርኝት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ነው ያሉት፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ችግር ፈቺ ምርምሮች ላይ ትኩረታቸውን በማድረግ የማህበረሰቡን ችግር በመፍታት በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ልማት ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎና አስተዋጽኦ ሊያደርጉ እንደሚገባም አመልክተዋል። ከዚህ አንጻር ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፋጠን ችግር ፈቺ ምርምሮች ላይ በማተኮር እያከናወናቸው የሚገኙ የምርምር ተግባራት ሞዴል መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ለማበረታታት ያቋቋመው የቢዝነስና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ማእከል የፈጠራ ሃሳቦች በልጽገው ወደ ተግባር የሚሸጋገሩበትን ምቹ የቴክኖሎጂ አውድ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው ማእከሉ የምርምር ሃሳብ ያላቸውን ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን በመቀበል ሃሳባቸውን ወደ መሬት የሚያወርዱበትን ምቹ የቴክኖሎጂ አውድ ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሰቲው ማእከሉን በቴክኖሎጂ፣ በባለሙያዎችና በዘመናዊ መሳሪያዎች በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገባ ማድረጉን ጠቁመው ስራ ፈጣሪዎች ምርምርና የፈጠራ ሃሳባቸው አድጎ ወደ ገበያ እንዲወጣ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡ ማእከሉ ችግር ፈቺ የምርምር ሃሳቦች ከመደርደሪያ ወርደው ወደ ኢንዱስትሪዎችና ካምፓኒዎች እንዲሸጋገሩ ብሎም የማህበረሰቡን ችግር መፍታት እንዲችሉ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር በመግለጽ። በማእከሉ የምረቃ ስነ ስርአት ላይ የአፍሪካ ልህቀት ማእከል ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብረሃን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።
በሐረሪ ክልል ከ38 ሺ 300 በላይ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደዋል- የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ
Jun 5, 2026 628
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ከ38 ሺ 300 በላይ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ጀማል ኢብራሂም ገለጹ። የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ ጀማል ኢብራሂም በሰጡት መግለጫ፤ የኮደርስ ሥልጠናው የዜጎችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት በማዳበር ረገድ እንደ አገር የተጀመረውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማሳለጥ ትልቅ እገዛ አለው ብለዋል። እስካሁን በኢኒሼቲቩ በተከናወነው ስራ በክልል ደረጃ ስልጠናውን ካጠናቀቁ ወጣቶች መካከል 27 ሺህ 574 የሚሆኑት የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውንም ጠቁመዋል። በመርሐ ግብሩ ፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አንድሮይድና ተያያዥነት ያላቸው ስልጠናዎች እየተሰጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ሥልጠናው ወጣቶችን የክህሎት ባለቤት ከማድረግ ባለፈ፣ ብቁ፣ ተወዳዳሪና ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል። ሥልጠናው ወጣቶችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ዕድሉን ያላገኙ ወጣቶች በቀጣይ ተመዝግበው እንዲሰለጥኑም ጥሪ አቅርበዋል።
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ለተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ስኬት የጎላ ሚና አላቸው
Jun 5, 2026 688
ጎንደር፤ ግንቦት 28/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ለተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ስኬት የጎላ ሚና እንዳላቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። ጎንደር ዩኒቨርሲቲ "በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ በጤና፣ በኑሮና በስነ ምህዳር ላይ ዘላቂ አቅምን መገንባት" በሚል መሪ ሀሳብ 32ኛውን ዓመታዊ የምርምር ጉባኤ እያካሄደ ነው። ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በጉባኤው እንደገለጹት፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተገኘው ልምድና ተሞክሮ በመቀመር ለዲጂታል 2030 ግብ ስኬት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የላቀ አበርክቶ ሊኖራቸው ይገባል። በኢትዮጵያ እየተሰጠ ያለው የ5 ሚሊየን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወጣቱ ትውልድ የመጪው ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ እውቀት ባለቤት እንዲሆን አስቻይ ሁኔታን እንደሚፈጥርም አስረድተዋል። የዲጂታል መሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋት የተከናወኑ ተግባራት ለዲጂታል ኢኮኖሚው መጠናከር መሠረት መጣሉንም ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ ነው ብለዋል። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው በፈጣንና ተለዋዋጭ አለም ውስጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂን አስፈላጊነት በመረዳት ዩኒቨርሲቲው ምርምር ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በዚህም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ምርምርና የፈጠራ ስራዎችን በማበረታታት በዘርፉ ብቁ ተመራማሪዎችን ለማፍራት ትኩረት ተደርጓል ብለዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው ይህም ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ በይፋ ወደ ራስ ገዝነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት ያለመ መሆኑንም አመልክተዋል። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ የዘመኑ ትውልድ የወደፊቱን አለም መቀላቀል እንዲችል የዲጂታል ቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ባለቤት መሆን አለበት ብለዋል። በአለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አብዮት ኢትዮጵያ ተቀላቅላ መጓዝ ትችል ዘንድ ምሁራን በጥናትና ምርምር ማገዝ እንዳለባቸውም ገልጸዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ዓመታዊ የምርምር ጉባኤ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ተመራማሪዎች፣ መምህራንና ተማሪዎች በሚቀርቡ የምርምር ስራዎች ላይ እየተወያዩ ነው። በጉባኤው ላይ የተዘጋጀው የምርምርና የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽንም በዛሬው ዕለት ለእይታ ክፍት ተደርጓል።
ኢንስቲትዩቱ በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን ማስፈልፈል የሚያስችል ዘመናዊ የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል እያስገነባ ነው
Jun 5, 2026 644
ጋምቤላ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦የጋምቤላ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን ማስፈልፈል የሚያስችል የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል በማስገንባት ላይ መሆኑን አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ በጋምቤላ ከተማ ከ58 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ እያካሄደ ያለውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ሂደቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ ጎብኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ማዕከሉ የዶሮ እርባታውን ለማዘመንና ለማስፋት ዓይነተኛ ሚና ይኖረዋል። በተለይም እንደ ሀገር ጤናማ የአመጋገብ ስርዓትን ለማጠናከር እየተተገበረ ያለውን የሌማት ትሩፋት መርሃግብር ስኬታማ ለማድረግ የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በመሆኑም የግንባታውን ሂደት በማፋጠን ወደ ስራ ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ለማዕከሉ ግንባታ መፋጠን የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ያደርጋልም ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሯ። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሪያል ጂንግ፤ ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተሻሻሉ የእንስሳትና የዕጽዋት ዝርያዎችን በማውጣት ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ እያስገነባ ያለው የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል የተሻሻሉ ዝርያዎች ለአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች ተደራሽ ለማድረግ ያለም መሆኑንም ተናግረዋል። በምርምር ኢንስቲትዩቱ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ አብዮት አለማየሁ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ የማዕከሉ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባ በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን የማስፈልፈል አቅም አለው። በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፍ ከ58 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለው ማዕከሉ አሁን ላይ ግንባታው ከ80 ከመቶ በላይ መድረሱን ገልጸዋል። የማዕከሉን 2ኛ ምዕራፍ ግንባታንም ለማስጀመር የጨረታ ሂደቱ መጠናቀቁንና በቅርቡ ስራው እንደሚጀመር አቶ አብዮት ገልጸዋል።
ስፖርት
በ19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ጌታቸው ማስረሻና አትሌት መሰለች አለማየሁ አሸነፉ
Jun 7, 2026 214
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፦ 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ዛሬ ረፋድ ላይ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ ተካሂዷል። በወንዶች ውድድር የሸገር ሲቲው አትሌት ጌታቸው ማስረሻ አንደኛ በመውጣት በድል አጠናቋል። ባየልኝ ተሻገር ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ሁለተኛ፣ በላይ ጥላሁን ከአዲስ አበባ አትሌቲክስ ክለብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሴቶች የአዲስ አበባ ፖሊሷ መሰለች አለማየሁ አሸናፊ ሆናለች። ዝማም ባራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ የሸገር ሲቲዋ በቀለች ተኩ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። በ19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳታፊ ሆነዋል። የውድድሩ ዋና አላማ በዴንማርክ ኮፐንሃገን በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም ለሚካሄደው 26ኛው የዓለም አትሌቲክስ የግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች መምረጥ እና ተተኪዎችን ማፍራት ነው። በውድድሩ ላይ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ አትሌቶች የገንዘብ፣ሜዳሊያና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የዘንድሮው ውድድር ተሳታፊዎች ብዛት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የ434 አትሌቶች ጭማሪ ማሳየቱን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ዋልያዎቹ ድል ቀንቷቸዋል
Jun 6, 2026 786
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታ ኢትዮጵያ ማላዊን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍጹም ጥላሁን ጨዋታው በተጀመረ በአንደኛው ደቂቃ ግቧን አስቆጥሯል። ጨዋታው ተመጣጣኝ የሚባል ፉክክር ተደርጎበታል። ብሔራዊ ቡድኖቹ ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታቸውን ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ ስታዲየም ያደርጋሉ። ኢትዮጵያ ጨዋታውን የምታደርገው፣ የፊፋ ዓለም አቀፍ የብሔራዊ ቡድኖች የጨዋታ ቀናትን (FIFA Window) በመጠቀም መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
በሮም እና ሞስኮ የደመቁት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች
Jun 6, 2026 763
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሮምና በሞስኮ በተካሄዱ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ድል አስመዝግበዋል። የዘንድሮው የዝናሜንስኪ ሜሞሪያል አትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ደማቅ ድል የተመዘገበበት መድረክ ሆኗል። በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የ“F” ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ፣ የኢትዮጵያ አትሌቶች አስደናቂ ብቃት በማሳየት ውድድሩን በድል አጠናቀዋል። በሩሲያ ዋና ከተማ በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፥ በአራት የተለያዩ የርቀት ዓይነቶችም የወርቅ ሜዳሊያዎችን ማሸነፍ ችለዋል። በሴቶች የ1500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም ርቀቱን በ3:58.59 በሆነ ፈጣን ሰዓት በማጠናቀቅ አንደኛ ወጥታለች። አትሌት ሳሮን በርሄ በ4:01.96 ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። በዚሁ ውድድር ላይ አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ፣ እንዲሁም አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሴቶች የ10000 ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በ32:23.54 አንደኛ በመሆን ስታሸንፍ፣ አትሌት ቤተልሔም ኦላና በ32:25.57 ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። ሌሎቹ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታደለ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል። በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ውድድር፣ ብርቱ ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ርቀቱን በ9:36.20 በማጠናቀቅ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በሴቶች 800 ሜትር ውድድር አትሌት ሀብታም ገበየሁ በ2:02.53 በሆነ ሰዓት 6ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በወንዶች የ10,000 ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ እጅግ ግሩም ውጤት አስመዝግቧል። አትሌት እዮብ ርቀቱን በ27:55.75 በማጠናቀቅ ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቋል። በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ በ28:16.57 ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቅ ችሏል። በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል ውድድር አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ ርቀቱን በ8:35.32 አንደኛ በመሆን በበላይነት አሸንፏል። አትሌት ሂርኮ ኃይሉ በበኩሉ ርቀቱን በ8:38.24 በማጠናቀቅ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። የ2026 ዳይመንድ ሊግ አራተኛ መዳረሻ በሆነው የሮሙ የሴቶች 5000 ሜትር ውድድር፣ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ ሰባተኛ ያለውን ደረጃ በሙሉ በመቆጣጠር በበላይነት አጠናቀዋል። በውድድሩም አትሌት ልቅና አምባው በ14:18.41 የወቅቱን የዓለም ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ የባለድልነት ዘውዱን ደፍታለች። አትሌት ልቅና አምባው የግሏን ምርጥ ሰዓት ከዓምስት ሰከንድ በላይ ማሻሻል የቻለች ሲሆን፥ የወቅቱ የርቀቱ ፈጣን በሆነው 14:18.41 ሰዓት ውድድሩን አሸንፋለች። ይህች አትሌት ቀደም ሲል በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ የሚታወስ ነው። በዚሁ የሮም ውድድር አትሌት አለሚቱ ባወቀ በ14:18.54 ሁለተኛ እንዲሁም አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ በ14:18.94 ሶስተኛ በመሆን ውድድሩን ማጠናቀቃቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር ነገ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Jun 6, 2026 525
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር ነገ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ውድድሩን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። መነሻው እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድር ላይ በወንዶች 455፣ በሴቶች ደግሞ 183 በድምሩ 638 አትሌቶች እንደሚሳተፉ በመግለጫው ላይ ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን የውድድሩ ዋና አላማ በስዊድን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድሩ ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች መምረጥ እና ተተኪዎች ማፍራት ነው ብለዋል። የፌዴሬሽኑ ውድድር እና ተሳትፎ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ጊዜ አድነው በበኩላቸው በውድድሩ ላይ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ደረጃ ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶች የገንዘብ፣ የሜዳልያና የዋንጫ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው አመልክተዋል። የዘንድሮው ውድድር ተሳታፊዎች ብዛት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የ434 አትሌቶች ጭማሪ ማሳየቱን የፌዴሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።
አካባቢ ጥበቃ
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው ተግባራዊ የተደረጉ ፕሮጀክቶች ለአካባቢ ጥበቃ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
Jun 6, 2026 664
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ የወንዝ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማቶችን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው የተተገበሩ ፕሮጀክቶች ለአካባቢ ጥበቃ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ገለጸ። የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ53ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ ተከብሯል። ቀኑን ምክንያት በማድረግም ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ከተማ የተውጣጡ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የስራ ሀላፊዎች እና ባለሙያዎች ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ የተሰራውን የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቱ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ ክፍት መደረጉ ይታወሳል። የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው የተተገበሩ ፕሮጀክቶች የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው። በአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰው፤ ይህም የአየር ብክለት መቀነስን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች እያስገኘ ነው ብለዋል። ይህም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲቸራት ያስቻለ መሆኑን በመጠቆም፤ ሥነ ምህዳርን በማሻሻል በኩል ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም አብራርተዋል። የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ፕሮጀክት አካባቢ ጥበቃን ውጤታማ እያደረጉ ካሉ ሥራዎች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመው፤ የእንጦጦ ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ለዚህ አይነተኛ ማሳያ ነው ብለዋል። በፕሮጀክቱ ሀገር በቀል ዛፎች መተከላቸውን ጠቅሰው፤ ሀገር በቀል የኮንሶ የአካባቢ ጥበቃ እውቀቶች አሻራ ያረፈበት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም አንስተዋል። መሰል የአካባቢ ጥበቃና ልማት ሥራዎች ኢትዮጵያ ተምሳሌታዊና ተጠቃሽ ሀገር እያደረጋት ነው ሲሉም ዋና ዳይሬክተሯ አመላከተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ እሸቱ ለማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የእግረኛ መንገዶች፣የሳይክልና አማራጭ መንገዶችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በተሽከርካሪዎች ወደ አየር የሚለቀቀውን በካይ ጋዝ እንዲቀንስ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል። ፕሮጀክቱ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ለውጤት በቅቷል ከዚህ በኋላ ፕሮጀክቱ በሚጠበቀው ደረጃ አገልግሎት እንዲሰጥ ሕዝቡ ሊንከባከበው ይገባል ብለዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ዶኤ (ዶ/ር)፤ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያዊያን አቅም በአጭር ጊዜ ተገንብቶ ለውጤት መብቃቱ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ላይ ላላት ቁርጠኝነት መሰል የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ምስክሮች ናቸው ያሉት ተወካዩ ተፈጥሮን ከዘመናዊነት ጋር አጣጥሞ መሄድ ያለውን ውጤት አመላካች ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር ያስችላል
Jun 5, 2026 917
አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር የሚያስችል መሆኑን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን እና መሠረተ-ልማት ዲቪዚዮን ዳይሬክተር ሮበርት ሊሲንጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን በሚያሳልጡ በትራንስፖርት፣ ኢንዱስትሪ፣ ኃይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂዎች እና በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ነው፡፡ በዚህም በየዓመቱ ለነዳጅ የሚወጣውን ወጪ መቀነስና በታዳሽ ኃይል የሚመራ የትራንስፖርት ሥርዓት መገንባት የሚያስችል ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂና የትግበራ ዕቅድ ይፋ አድርጋለች፡፡ በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ኢኖቬሽን እና መሠረተ-ልማት ዲቪዚዮን ዳይሬክተር ሮበርት ሊሲንጌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂ ከዓለም አቀፍ የህግ ማዕቀፎች ጋር የተናበበ ነው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባ ነዳጅ ጥገኛ በመሆናቸው ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጭ እንደሚዳረጉ ገልጸው፤ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂና የትግበራ ዕቅድ ወጭን ከመቀነስ ባሻገር ለአስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ዋስትና ይሆናል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እያደረገች ያለችው ሽግግር የአየር ብክለትን በመቀነስ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት አጋዥ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር እስከ 2030 አዲስ ከሚመዘገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል 30 በመቶ የሚሆኑትን በሀገር ውስጥ ለማምረትና ለመገጣጠም ማቀዷ በአፍሪካውያን መካከል ያለውን የንግድ ትስስር ያጠናክራል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መጀመር ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚደረገውን ሽግግር ያሳልጣል ያሉት ዳይሬክተሩ፥ በአህጉሪቱ ያለውን የንግድ እሴት ሰንሰለት እንደሚያቀላጥፍም ገልጸዋል፡፡
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ
Jun 3, 2026 1324
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዮት አስታወቀ። የኢትዮጵያ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል። እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል። የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል። በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ይሆናል። በመደበኛ ሁኔታ ወቅታዊው የክረምት ዝናብ ቀደም ብሎ በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ አጋማሽ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚጀምር ሲሆን፤ በሂደት እየተጠናከረ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ አካባቢዎች እንደሚስፋፋም ገልጿል። በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛውና በምስራቅ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ዝናቡ በመጠንም ሆነ በስርጭት የተሻለ እንደሚሆን ይጠበቃል ብሏል። የሚኖረው እርጥበት ለግብርና ስራ የማሳ ዝግጅት እና የመኸር ሰብሎችን ለመዝራት እንዲሁም ለበልግ ሰብል ተጠቃሚ አካባቢዎች መልካም አጋጣሚ እንደሚኖረው ጠቁሟል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የአገሪቱ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው የገጽምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው ይጠበቃል ብሏል። በዚህም በመካከለኛው እና ታችኛው አባይ፣ ላይኛው እና መካከለኛ ባሮ አኮቦ፣ ላይኛው ስምጥ ሸለቆ፣ ኦሞ ጊቤ፣ አዋሽ እንዲሁም ገናሌ ዳዋ ከመካከለኛ እስከ ከባድ የገጸ ምድር ውሃ ፍሰት ይኖራቸዋል ብሏል። በላይኛው አባይ፣ ኦጋዴን፣ መካከለኛው አዋሽ፣ ስምጥ ሸለቆ እና ኦሞ ጊቤ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸውም ገልጿል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማ ማህበረሰብን ለመፍጠር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው
Jun 3, 2026 1117
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማ ማህበረሰብን ከመፍጠር አኳያ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሸጋው ፈንታዬ ገለጹ። ማህበሩ እነዚህን ስራዎች የሚደግፉ የምርምር፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ምቹ የአየር ፀባይ ሁኔታ እና ንጹህ አካባቢዎችን ለማስፋፋት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ፣ በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄና ሌሎች መርሃ ግብሮች በተከናወኑ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ ነው። የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሸጋው ፈንታዬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ጤናማ ማኅበረሰብን ለመፍጠር ለዜጎች ተስማሚ የሆነ የመኖሪያ አካባቢን መፍጠር ይጠይቃል። የደኖች ጭፍጨፋ እንዲሁም የአካባቢን ንጽህና አለመጠበቅ የዜጎች ጤና ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር አንስተዋል። በኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት ተግባራዊ የተደረጉት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እንዲሁም የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ስራዎች የአካባቢ ጤናን በመጠበቅ ለማኅበረሰብ ጤና ጉልህ አስተዋጽኦ አላቸው ብለዋል። የአካባቢን ንጽህና መጠበቅ ዜጎችን ከተለያዩ በሽታዎች እንደሚጠብቅም አክለዋል። የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማኅበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ስራዎች ላይ ገንቢ ሚና በመጫወት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ማህበሩ እነዚህን ስራዎች የሚደግፉ የምርምር፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አለማየሁ ሀዲስ በበኩላቸው፤ የአየር ንብረት ለውጥ መዛባት እና የአካባቢ ንጽህናን አለመጠበቅ በዜጎች ጤና ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ለመከላከል የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን እና አካባቢን ንጹህ ለማድረግ የሚሰሩ ተግባራትን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራን የአካባቢን ጤና ለመጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን ሊያጠናክሩ ይገባል ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 4869
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 5047
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 3883
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 3787
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 3155
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 4513
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው። መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል። በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል። ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል። በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል። በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ። በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 4109
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 4339
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Jun 7, 2026 571
ባሳለፍነው ሳምንት … ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባሳለፍነው ሳምንት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተካሂዷል። ድምፅ ለመስጠት 54 ሚሊየን 57 ሺህ 861 መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማሳወቁ ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለመራጮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምርጫው ወቅት ድምጽ ስለሰጡ መራጮች ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ማገልገል መታደል መሆኑን ገልጸው፤ ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይህንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ ሲሉም አስገንዝበዋል። ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ሥራ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 22 ነጥብ 25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን ይሸፍናል። ይህ ፕሮጀክት የማይቆራረጥ የልማት ሥራችን ኅያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሀገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና 73 አባላት ከያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል። ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ከአኅጉራችን ነባራዊ ሁኔታና ተሞክሮ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ አፍሪካዊ ተቋማት ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የምርጫ ሂደታችንን ለመደገፍ በመላው ሀገሪቱ ታዛቢዎችን በማሰማራት የምርጫ ታዛቢ ልዑኩ ላደረገው ያልተቆጠበ ጥረት እውቅና እና አድናቆት እየሰጠን፤ የምልከታውን የተሟላ ውጤት እንጠብቃለን ሲሉም አመላክተዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻ ልማት፤ የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳን የያዘ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽንም፤ ከወንዞቹ ባሻገር እስከ 50 ሜትር የሚዘልቅ መሆኑን አስረድተዋል። የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን እና የንግድ ቦታዎችን ልማት ማካተቱን ጠቅሰው፤ ከተማዋን በእጅጉ የቀየረ ነው ብለዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን ገጽታ እና አገልግሎት ከማሻሻል ባለፈ በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስ እና በተያያዙ ዘርፎች ለብዙ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም አብራርተዋል። አብዛኛው ሥራ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች መቀረጹና መተግበሩ፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት እና በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው ዐቅም እያደገ መምጣቱን ያሳያል ነው ያሉት። ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎች እና ቆሻሻዎች የሚጣሉባቸው፣ በወንዝ ዳርቻዎች በሚኖሩ ማኅበረሰቦች ላይ የጎርፍ አደጋ ይጋርጡ የነበሩት እነዚህ አካባቢዎች፤ አሁን ላይ ወደ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ለሕይወት ምቹ ወደሆነ የከተማ ቦታነት እየተቀየሩ መሆኑንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ሁኔታም፤ የንግድ እና የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ከዚህ ቀደም ከነበረው ያልተናበበ ሥራ ተላቀው በጥናትና በጋራ ግብ ተባብሮ መሥራት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ስለመሆኑ አመላክተዋል። ይህ ፈጣን የልማት ሥራ አዲስ አበባን አረንጓዴ፣ ይበልጥ የተሳሰረች፣ በኢኮኖሚ ንቁ እና ሰውን ማዕከል ያደረገች ከተማ የማድረግ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ላይ መሰረት የተጣለበት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ
በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ …
Jun 3, 2026 1959
በዮሐንስ ደርበው በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር ሞላወርቅ አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በዓለምም ሆነ በሀገራችን አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው የደም ግፊት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በቆይታቸውም፤ ለደም ግፊት አጋላጭ ስለሆኑ ምክንያቶችና ሊደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄም እንዲሁም ከመድሃኒት አወሳሰድ ጋር በተያያዘ ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አቅርበዋል። · የደም ግፊት ምንድን ነው? ደም በደም ሥሮቻችን ሲያልፍ፤ የሚለካው መጠን “የደም ግፊት” እንደሚባል ዶክተር ሞላወርቅ ያስረዳሉ። የላይኛው (ሲስቶሊክ ወይም ከፍተኛው) የደም ግፊት መጠን ልብ በምትኮማተርበት ጊዜ ደም ወደ ደም ሥር ሲረጭ የሚለካው መሆኑንም ይገልጻሉ። የታችኛው (ዲያስቶሊክ ወይም ዝቅተኛው) የደም ግፊት መጠን ደግሞ ልብ ደም ለመቀበል ለአፍታ ዕረፍት በምታገኝበት ጊዜ የሚከሰት የግፊት ደረጃ መሆኑንም ይገልጻሉ። · የደም ግፊት ደረጃዎች እና ማስጠንቀቂያቸው ዶክተር ሞላወርቅ እንደሚሉት፤ የጤናማ ሰው የደም የግፊት መጠን 120 በ 80 እና በታች መሆን ይኖርበታል። በሌላ በኩል ግን ይላሉ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 የታችኛው ደግሞ ከ80 በታች ከሆነ “ከፍ ያለ ወይም የጨመረ የደም ግፊት ደረጃ” ይባላል። የላይኛው ከ130 እስከ 139 ወይም የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከሆነ ደግሞ “ደረጃ አንድ የደም ግፊት” እንደሚባል ያስረዳሉ። የላይኛው ከ140 በላይ ሲሆን እና የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ ደግሞ “ደረጃ ሁለት የደም ግፊት” እንደሚባል ነው የሚገልጹት። በሌላ በኩል “የከፋ የደም ግፊት ደረጃ” የሚባል እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም የላይኛው ከ180 በላይ እና የታችኛው ከ120 በላይ ሲሆን ነው በማለት ያብራራሉ። · ለደም ግፊት መጨመር መንስዔዎቹ ምንድን ናቸው? በዋናነት ሁለት ዓይነት የደም ግፊት መኖሩን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ ከፍተኛ የደም ግፊት እና መንስዔው የሚታወቅ የደም ግፊት መሆኑን አስረድተዋል። በዋናነት ወይም በአብዛኛው ከ90 እስከ 95 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ደም ግፊት የሚባለው መሆኑን ገልጸው፤ በርካታ መንስዔዎች ሊኖሩት እንደሚችሉ ቢገመትም ሁሉም በውል እንደማይታወቁ ያነሳሉ። ከበርካታ መንስዔዎቹ መካከልም፤ በቤተሰብ የሚወረስ (ተላላፊ)፣ አካባቢያዊ ምክንያቶች እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ የሚሉት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። የአኗኗር ዘይቤ ሲባልም፤ የአመጋገብ ሥርዓት በተለይም ጨው የበዛበት ምግብ፣ ክብደት መጨመር፣ አካባቢያዊ ሁኔታዎች (አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ)፣ የስኳር ታማሚ መሆን የሚሉት ይጠቀሳሉ ይላሉ። · ለደም ግፊት በተለይም እነማን ተጋላጭ ናቸው? ዕድሜ በጨመረ ቁጥር የደም ግፊት የመከሰት ዕድሉም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በዚህም መሠረት ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ይናገራሉ። እንዲም በቤተሰብ የደም ግፊት ኬዝ ያለባቸው ሰዎች፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒክ ግሩፕ) ለምሳሌ፡- በጥቁሮች (አፍሪካውያን)፣ በኤስያውያን፣ በደቡብ ኤስያውያን ላይ ከፍተኛ የደም ግፊት ሊከሰት እንደሚችል ይገልጻሉ። እንደ ዶክተር ሞላወርቅ ማብራሪያ፤ በአጠቃላይ አጋላጭ ምክንያቶች በሁለት ተከፍለው ሊታዩ ይችላሉ። አንደኛው፡- ልንከላከላቸው (ልንቀንሳቸው) የምንችላቸው መሆናቸውን በመግለጽ ይህም የአመጋገብ ሥርዓትን ማስተካከል፣ ክብደት መቀነስ፣ አልኮልና ሲጋራ ማቆም እና መሰል መሆናቸውን አብራርተዋል። ሁለተኛው፡- ልንከላከላቸው የማንችላቸው መሆናቸውን ገልጸው ይህም፤ የዕድሜ መጨመር፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒሲቲ) እና በቤተሰብ የሚተላለፍ የሚሉትን ጠቅሰዋል። · የደም ግፊትን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? የደም ግፊ ከተከሰተ መቆጣጠር እንጅ ማዳን እንደማይቻል ገልጸው፤ ከላይ እንደተጠቀሰው አስቀድሞ መከላከል ወይም ማዘግየት የሚቻል እና መከላከል የማይቻል የደም ግፊት ደረጃ መኖሩን አስረድተዋል። · የደም ግፊት በውል የሚታወቅ ምልክት አለው? የደም ግፊት ሲከሰት ምልክት እንደሌለው በማንሳት፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ “ዝምተኛው ገዳይ” እስከመባል መድረሱን ዶክተር ሞላወርቅ ያነሳሉ። ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ግን፤ በአንድ ወይም በሁለት የሰውነት አካል ላይ ችግር ሊደርስ እንደሚችል ከዚህም ሲያልፍ እስከ ሞት እንደሚያደርስ ይጠቅሳሉ። በተያያዘም፤ የራስ ምታት፣ የዐይን ብዥ ብዥ ማለት፣ ትንፋሽ ማጠር፣ የድካም ስሜት፣ አንገት የመያዝ ዓይነት ስሜቶች የደም ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ሊስተዋሉ የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል። አክለውም፤ በአብዛኛው በሕብረተሰቡ ላይ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርስና ድንገት በጨመረ ጊዜ፤ ለሞት፣ ለአደጋ፣ ለልብ ድካም፣ አጣዳፊ ለሆነ የልብ ህመም፣ በጭንቅላት ላይ የደም መፍሰስ፣ የኩላሊት ድክመት፣ በደም ሥሮች በአግባቡ ደም እንዳይተላለፍ ማድረግ፣ ለዐይነ ስውርነት መዳረግን ጨምሮ መሰል ጉዳቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝበዋል። · መድኃኒት አወሳሰድ ላይ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ ዶክተር ሞላወርቅ እንደገለጹት፤ አንድ ሰው ደም ግፊት እንዳለበት ከተነገረው በኋላ ሕክምናውም እንደ ደም ግፊቱ ደረጃ ይለያያል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 ከሆነ “የጨመረ ግፊት” ይባላል፤ እዚህ ላይ ሰውየው ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አመጋገቡን እንዲያስተካክል፣ ስፖርት እንዲሠራ፣ ክብደት እንዲቀንስ፣ ሱስ (ሲጋራ፣ አልኮል) እንዲቀንስ ክትትል ይደረጋል ብለዋል። ስለዚህ መድኃኒት ሳይጀምር የአኗኗር ዘይቤን በማስተካከል የደም ግፊቱን ሊቀንሰው (ሊቆጣጠረው) ይችላል ማለት ነው ሲሉም ይገልጻሉ። “ደረጃ አንድ ግፊት” የሚለው ላይ ከደረሱ ግን ሕክምና የሚጀምሩም የማይጀምሩም እንዳሉ ተናግረዋል። ይህም ማለት የላይኛው ከ130 እስከ 139 የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከደረሰ ሕክምና የሚጀምሩት የስኳር ህመም ያለባቸው፣ የስትሮክ ህመም ያለባቸው፣ ከልብና ደም ሥር የተገናኙ ህመሞች ያሉባቸው ከሆኑ ቢያንስ አንድ የግፊት መድኃኒት መጀመርና ክትትል ማድረግ አለባቸው ይላሉ። በሌላ በኩል ግን ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ ሰዎች “ደረጃ ሁለት ግፊት” ላይ ከደረሱ (የላይኛው ከ140 የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ) ሁሉም መድኃኒት መጀመር እንዳለባቸው በአጽንዖት ገልጸዋል። የሚጀምሩት መድኃኒትም አሁን ባለው በተሻሻለው የሕክምና ዘይቤ ሁለት መድኃኒቶች የሚጀምሩበት ሁኔታ እንዳለ ነው የሚያስረዱት። የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ግን ለሁሉም የግፊት ዓይነቶች መሠረት (የሚመከር) መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ መድኃኒት ጀምሬያለሁ ብሎ የአኗኗር ዘይቤው ላይ ቸልተኝነት ሊኖር እንደማይገባም ነው የሚመከሩት። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከግፊት ጋር በተያያዘ ወደ ሆስፒታል መጥተው የሚታከሙ ታካሚዎች አብዛኞቹ፤ ጀምረው ያቋረጡ፣ ለመጀመር ፍላጎት የሌላቸው፣ ቅድመ ምርመራ ባለማድረግ ምክንያት ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ የተጎዱ ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። ስለዚህ የግፊት መድኃኒት ከተጀመረ ሊቋረጥ እንደማይችል አስጠንቅቀዋል። በየጊዜው ክትትል ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በሂደት እንደ ግፊቱ ሁኔታ መድኃኒቶች ሊቀነሱም ሊጨመሩም እንደሚችሉ አመላክተዋል። · የመስፋፋት ደረጃ የዓለም ጤና ድርጅት በ2024 ያወጣውን መረጃ ዋቢ አድርገው፤ 1/3ኛው የዓለም ሕዝቦች በደም ግፊት እንደሚጠቁ ዶክተር ሞላወርቅ አንስተዋል። ከእነዚህ መካከልም፤ 7 ነጥብ 6 ሚሊየን ገደማው በአንድም በሌላም ምክንያት ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ጠቁመዋል። አብዛኞቹ የደም ግፊት ታማሚዎች ቁጥር የሚመዘገበው ደግሞ በመካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ሀገራችንን ያካትታል ሲሉ ገልጸዋል። በሀገራችን ደረጃም ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ባይኖሩም ከግፊት ጋር በተያያዘ በ2001 ላይ በ35 ሳይቶች የተጠኑ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከ21 እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ በደም ግፊት የሚጠቃ ነው ይላሉ። በአብዛኛው ደግሞ ከተማ ላይ እንደሚበዛ ጠቁመው፤ በተለይም አዲስ አበባ ላይ እስከ 30 በመቶ እንደሚደርስ የጥናቶቹ ውጤቶች ማመላከታቸውን ተናግረዋል። አብዛኞቹ ኬዞች ደግሞ ዕድሜያቸው ከፍ ያለ፣ ክብደታቸው የጨመረ፣ አልኮል እና ሲጋራ የሚጠቀሙ እና የስኳር ህመም ያለባቸው ሰዎች ጋር የሚገናኙ መሆናቸውን አስረድተዋል። እንደ ዓለም አቀፍ ደረጃም ኬዙ ካለባቸው መካከል ግማሽ ያህሉ ግፊት እንዳለባቸው እንኳን እንደማያውቁ ነው የሚገልጹት። ለግፊት ሕክምና ትክክለኛ ክትትል አድርገው ግፊታቸውን በአግባቡ የሚቆጣጠሩት ከ 5 ሰዎች 1 መሆኑንም ጥናቶች ያሳያሉ ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ በሀገራችን በሕብረተሰቡ ዘንድ ለደም ግፊት መለካት ኬዙ ከተገኘም የሕክምና ክትትል የማድረግ ሁኔታዎች ዝቅተኛ መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ሕብረተሰቡ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከአካል ጉዳት እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል ተገንዝቦ፤ የደም ግፊቱን የመለካት ልምምዱን ሊያዳብር እንደሚገባ ዶክተር ሞላወርቅ መክረዋል። በሌላ በኩል እንደ ሀገራችን ባሉ ሆስፒታሎች በጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ ወይም መቋረጥ (ስትሮክ) ካለባቸው ሰዎች ከ70 እስከ 85 በመቶው ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ የሚከሰት መሆኑን ገልጸው፤ ድንገተኛ ግፊት መጨመር ከልብ እና ከደም ሥሮች ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዓለምም ሆነ እንደ ሀገር አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንደኛው ግፊት መሆኑንም አረጋግጠዋል። ስለዚህ የደም ግፊትን መለካት፣ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል፣ ከሱስ መራቅ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር ለጤናማ ሕይወት ከፍተኛ ሚና እንዳለው መክረዋል።
ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 5087
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 2827
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 11749
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 6628
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 12400
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 10875
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 3155
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 5646
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !