ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
መምህራን ለትውልድ ግንባታ ያላቸው አበርክቶ በመንግስትና በሕዝብ ዘንድ ትልቅ ክብር የሚሰጠው ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Feb 4, 2026 20
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፡- መምህራን ለሀገርና ለትውልድ ግንባታ ያላቸው አበርክቶ በመንግስትና በሕዝብ ዘንድ ትልቅ ክብር የሚሰጠው መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ የሚገኙ መምህራን የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን የመምህራን የመኖሪያ መንደር ግንባታ በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል።   በዚህም በ57 ማኅበራት የተደራጁ 6 ሺህ 194 መምህራንን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሲሆን፤ ተጠቃሚዎቹ የቤቱን ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ አስቀድመው የቆጠቡ ናቸው። ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ለመኖር ምቹ እና ለጎብኚዎች ሳቢ እየሆነች መጥታለች። ይህንን ዕድገት ተከትሎ የሚመጣውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ አማራጮች የቤት ግንባታዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በርካታ ቤቶች ተገንብተው ለተጠቃሚዎች ማስተላለፍ ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ ዛሬ ደግሞ የሀገር ግንባታ ምሰሶ ለሆኑት መምህራን ልዩ ትኩረት በመስጠት ይህን ግንባታ ጀምረናል ብለዋል። በማህበር ቤት ግንባታ መምህራን ፋና ወጊዎች ናቸው ያሉት ከንቲባዋ መምህራኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ 4 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ በመቆጠብ አስደናቂ ውጤት አስመዝግበዋል ነው ያሉት።   አስተዳደሩ ለመጀመሪያው ዙር የሚውል 40 ሄክታር መሬት ለመምህራኑ ያዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው መምህራን ሀገርን ለመገንባት ለሚከፍሉት ዋጋ በመንግስትና በህዝብ ዘንድ ያለውን ክብር በተግባር ያሳየንበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ትምሀርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዛሬው ዕለት በ57 ማህበራት የተደራጁ 6ሺህ 194 መምህራን የግንባታ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ መምህራን የትውልድ ቀራጭ፣ የሀገር ግንባታና የብልፅግና መሰረት በመሆናቸው ለሙያው የሚገባውን ክብር ለመስጠት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።   የመምህራንን የቤት ችግር በዘላቂነት መፍታት ሙሉ ትኩረታቸውን በትምህርት ጥራትና በትውልድ ግንባታ ላይ እንዲያደርጉ ማስቻል ነው ብለዋል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ ቤቶቹ በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ተገንብተው ለተጠቃሚዎች እንዲቀርቡ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ፤ አስተዳደሩ ለመምህራን ትኩረት በመስጠት የቤት ጥያቄያቸውን የሚመልሥ ተጨባጭ ተግባር እያከናወነ በመሆኑ ምስጋናቸውን ገልጸዋል። ይህ ምላሽ በመምህራን ዘንድ ለዓመታት የቆየውን የኑሮ ጫና የሚቀንስና በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ የተሻለ መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን የሰጡ መምህር እንዳልካቸው ደጀኔ፣ መምህር መስከረም ጎቤና እና መምህር ደለለኝ አስማሬ መምህራኑ ለረጅም ጊዜ ሲያቀርቡት የነበረው የቤት ጥያቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአስተዳደሩ ምላሽ በማግኘቱ አመስግነዋል።
የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን ደርሷል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Feb 4, 2026 26
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተገኝተው በመንግሥት የ6 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የዲጂታል ዘርፉ በተለይም የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አንስተዋል። ለውጡ ሲመጣ የሞባይል ተጠቃሚዎች ቁጥር 37 ሚሊዮን እንደነበር በመጥቀስ፥ አሁን ላይ በኢትዮ ቴሌኮም 87 ሚሊዮን በሳፋሪ ኮም ከ10 ሚሊዮን በላይ በድምሩ 97 ሚሊዮን የሞባይል ተጠቃሚዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ከለውጡ ወዲህ በ60 ሚሊዮን መጨመሩን ያሳያል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ሆኖም ይህ በቂ እንዳልሆነና እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሞባይል ተጠቃሚ እንዲሆን መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል። የ4 ጂ እና 5 ጂ ኔትወርክ አገልግሎት ተደራሽነት እየተስፋፋ መሆኑን አንስተው፥ 1 ሺህ 70 ከተሞች የ4 ጂ እንዲሁም 28 ከተሞች የ5 ጂ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህም ዜጎች የተሳለጠ ንግድና አገልግሎት እንዲያገኙ እያስቻለ ነው ብለዋል። በፋይናንስ ዘርፉ ከሦስት ዓመታት ወዲህ በሞባይል የገንዘብ ዝውውር የሚፈጽሙ ዜጎች ቁጥር 58 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ግብይት ስርዓቱም በጥሬ ገንዘብ ከሚደረግ ግብይት መብለጡን ጠቅሰው፥ ይህ የኢትዮጵያ የዝላይ ጉዞ የፖሊሲ ውጤት ስለመሆኑ አንስተዋል። በዲጂታል ክፍያ አገልግሎትም ባለፉት ስድስት ወራት የተመዘገበው ውጤት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነጻጸር በ60 በመቶ መጨመሩን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ገንዘብ ቁጠባና ብድር አገልግሎትም ማደጉን ነው ያስረዱት።  
በኮምቦልቻ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Feb 4, 2026 31
ኮምቦልቻ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ኮምቦልቻ ከተማ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። በኮምቦልቻ ከተማ ከሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነቡ ካሉ የልማት ፕሮጀክቶች ሶስቱ ተጠናቀው ለምረቃ በቅተዋል። የኮምቦልቻ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወንድወሰን ልሳነወርቅ በወቅቱ እንደገለጹት፣ በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን ከማምጣት ጎን ለጎን ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተፋጠነ ነው። በበጀት ዓመቱ በአቅመ ደካማ ዜጎች ቤት ግንባታ፣ በተማሪዎች ምገባ፣ የመስሪያና መሸጫ ሼዶች ግንባታን ጨምሮ ገበያን በማረጋጋት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ክትትልና ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል ። በከተማ አስተዳደሩ የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሲሳይ አየለ በበኩላቸው፣ በከተማዋ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የመንገድ፣ የትምህርት ቤት፣ የጤና ተቋማት እንዲሁም የውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል። ከሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነቡ ካሉ የልማት ፕሮጀክቶች ውስጥ የሰባት ነጥብ አምስት ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ፣ 45 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥና ሁለት ኪሎ ሜትር የኮብል ስቶን መንገድ ይገኝበታል ብለዋል። ዛሬ ግንባታቸው ተጠናቆ ለምረቃ የበቁት የወጣቶች መዝናኛ ሥፍራዎች፣ የመስሪያና የመሸጫ ሼዶች እንዲሁም የትምህርት ቤት መጸዳጃ ቤቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። አስተያየት ከሰጡት መካከል መሀመድ ሲራጅ እና አምሳለ ሀብታሙ የልማት ፕሮጀክቶቹ ለከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ አላቸው ብለዋል። በከተማዋ የሕብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በወቅቱ ተጠናቀው ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
የሚታይ
መምህራን ለትውልድ ግንባታ ያላቸው አበርክቶ በመንግስትና በሕዝብ ዘንድ ትልቅ ክብር የሚሰጠው ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Feb 4, 2026 20
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፡- መምህራን ለሀገርና ለትውልድ ግንባታ ያላቸው አበርክቶ በመንግስትና በሕዝብ ዘንድ ትልቅ ክብር የሚሰጠው መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ የሚገኙ መምህራን የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን የመምህራን የመኖሪያ መንደር ግንባታ በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል።   በዚህም በ57 ማኅበራት የተደራጁ 6 ሺህ 194 መምህራንን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሲሆን፤ ተጠቃሚዎቹ የቤቱን ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ አስቀድመው የቆጠቡ ናቸው። ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ለመኖር ምቹ እና ለጎብኚዎች ሳቢ እየሆነች መጥታለች። ይህንን ዕድገት ተከትሎ የሚመጣውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ አማራጮች የቤት ግንባታዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በርካታ ቤቶች ተገንብተው ለተጠቃሚዎች ማስተላለፍ ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ ዛሬ ደግሞ የሀገር ግንባታ ምሰሶ ለሆኑት መምህራን ልዩ ትኩረት በመስጠት ይህን ግንባታ ጀምረናል ብለዋል። በማህበር ቤት ግንባታ መምህራን ፋና ወጊዎች ናቸው ያሉት ከንቲባዋ መምህራኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ 4 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ በመቆጠብ አስደናቂ ውጤት አስመዝግበዋል ነው ያሉት።   አስተዳደሩ ለመጀመሪያው ዙር የሚውል 40 ሄክታር መሬት ለመምህራኑ ያዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው መምህራን ሀገርን ለመገንባት ለሚከፍሉት ዋጋ በመንግስትና በህዝብ ዘንድ ያለውን ክብር በተግባር ያሳየንበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ትምሀርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዛሬው ዕለት በ57 ማህበራት የተደራጁ 6ሺህ 194 መምህራን የግንባታ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ መምህራን የትውልድ ቀራጭ፣ የሀገር ግንባታና የብልፅግና መሰረት በመሆናቸው ለሙያው የሚገባውን ክብር ለመስጠት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።   የመምህራንን የቤት ችግር በዘላቂነት መፍታት ሙሉ ትኩረታቸውን በትምህርት ጥራትና በትውልድ ግንባታ ላይ እንዲያደርጉ ማስቻል ነው ብለዋል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ ቤቶቹ በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ተገንብተው ለተጠቃሚዎች እንዲቀርቡ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ፤ አስተዳደሩ ለመምህራን ትኩረት በመስጠት የቤት ጥያቄያቸውን የሚመልሥ ተጨባጭ ተግባር እያከናወነ በመሆኑ ምስጋናቸውን ገልጸዋል። ይህ ምላሽ በመምህራን ዘንድ ለዓመታት የቆየውን የኑሮ ጫና የሚቀንስና በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ የተሻለ መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን የሰጡ መምህር እንዳልካቸው ደጀኔ፣ መምህር መስከረም ጎቤና እና መምህር ደለለኝ አስማሬ መምህራኑ ለረጅም ጊዜ ሲያቀርቡት የነበረው የቤት ጥያቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአስተዳደሩ ምላሽ በማግኘቱ አመስግነዋል።
የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን ደርሷል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Feb 4, 2026 26
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተገኝተው በመንግሥት የ6 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የዲጂታል ዘርፉ በተለይም የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አንስተዋል። ለውጡ ሲመጣ የሞባይል ተጠቃሚዎች ቁጥር 37 ሚሊዮን እንደነበር በመጥቀስ፥ አሁን ላይ በኢትዮ ቴሌኮም 87 ሚሊዮን በሳፋሪ ኮም ከ10 ሚሊዮን በላይ በድምሩ 97 ሚሊዮን የሞባይል ተጠቃሚዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ከለውጡ ወዲህ በ60 ሚሊዮን መጨመሩን ያሳያል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ሆኖም ይህ በቂ እንዳልሆነና እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሞባይል ተጠቃሚ እንዲሆን መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል። የ4 ጂ እና 5 ጂ ኔትወርክ አገልግሎት ተደራሽነት እየተስፋፋ መሆኑን አንስተው፥ 1 ሺህ 70 ከተሞች የ4 ጂ እንዲሁም 28 ከተሞች የ5 ጂ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህም ዜጎች የተሳለጠ ንግድና አገልግሎት እንዲያገኙ እያስቻለ ነው ብለዋል። በፋይናንስ ዘርፉ ከሦስት ዓመታት ወዲህ በሞባይል የገንዘብ ዝውውር የሚፈጽሙ ዜጎች ቁጥር 58 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ግብይት ስርዓቱም በጥሬ ገንዘብ ከሚደረግ ግብይት መብለጡን ጠቅሰው፥ ይህ የኢትዮጵያ የዝላይ ጉዞ የፖሊሲ ውጤት ስለመሆኑ አንስተዋል። በዲጂታል ክፍያ አገልግሎትም ባለፉት ስድስት ወራት የተመዘገበው ውጤት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነጻጸር በ60 በመቶ መጨመሩን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ገንዘብ ቁጠባና ብድር አገልግሎትም ማደጉን ነው ያስረዱት።  
አስተዳደሩ የመዲናዋን የቤት አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ልዩ ልዩ የቤት ግንባታ አማራጮችን ተግባራዊ ማድረጉን አጠናክሮ ይቀጥላል
Feb 4, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት አቅርቦት ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ልዩ ልዩ አማራጮችን ተግባራዊ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ የሚገኙ መምህራን የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን የመምህራን የመኖሪያ መንደር ግንባታ በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል።   በዚህም በ57 ማኅበራት የተደራጁ 6ሺህ 194 መምህራንን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሲሆን፤ ተጠቃሚዎቹ የቤቱን ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ አስቀድመው የቆጠቡ ናቸው። ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ለመኖር ምቹ እና ለጎብኚዎች ሳቢ እየሆነች መጥታለች።   ይህንን ዕድገት ተከትሎ የሚመጣውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ አማራጮች የቤት ግንባታዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በርካታ ቤቶች ተገንብተው ለተጠቃሚዎች ማስተላለፍ ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ ዛሬ ደግሞ የሀገር ግንባታ ምሰሶ ለሆኑት መምህራን ልዩ ትኩረት በመስጠት ይህን ግንባታ ጀምረናል ነው ያሉት። መምህራን በማኅበር ተደራጅተውና ተገቢውን ቁጠባ በማድረግ የዕድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም ተናግረዋል።   አስተዳደሩ ለግንባታው የሚውል ከሊዝ ነፃ 40 ሄክታር መሬት ማዘጋጀቱን ገልጸው፤ ግንባታው በአጠረ ጊዜ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ የሆኑ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉ ይደረጋል ብለዋል። መምህራን ሀገርን በመገንባትና ትውልድን በመቅረጽ በኩል እያበረከቱት ያለውን የማይተካ ሚና አድንቀው፤ ይህ የመኖሪያ መንደር ግንባታ ሲጠናቀቅ የመምህራንን የኑሮ ጫና ከመቀነስ ባለፈ፤ በትምህርት ጥራት ማስጠበቅ ላይ የሚኖራቸውን ተነሳሽነት ያሳድጋል ነው ያሉት።
የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ የምታስተናግዳቸው አህጉራዊ ሁነቶች
Feb 4, 2026 168
በሙሴ መለሰ የዓለም ስርዓት በፍጥነት እየተቀያየረ ይገኛል። አፍሪካ በዚህ ተለዋዋጭ ስርዓት ውስጥ የሚገባትን ቦታ የመያዝ ጉዳይ የመነጋገሪያ አጀንዳ ከሆነ ሰነባብቷል። አፍሪካ በርካታ ወጣት የያዘች እና ብዝሃ የተፈጥሮ ፀጋዎች ያሏት አህጉር ናት። በአፍሪካ ተግባራዊ የተደረገው አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በቀጣናው የንግድ ትስስርን በማሳለጥ እድገትን የማፋጠን ተስፋ ተጥሎበታል። አፍሪካ እድሎቿን በሚገባ ለመጠቀምና የሚስተዋሉ ፈተናዎቿን ለመሻገር ምላሽ የምትሰጥበት የልማት እና እድገት ጉዞዋን ከመበየን ባለፈ በዓለም መድረክ የሚኖራትን ሚናም ይወስናል። በአህጉር ደረጃ የተቀመጡ እንደ አጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ያሉ አህጉራዊ ማዕቀፎች እንዲሳኩ ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። መንግስታት፣ የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮች ትብብራቸው ማጠናከር ይኖርባቸዋል።   የተገቡ ቃልኪዳኖችን ወደ ሚለካ ውጤት ለመቀየር ዘላቂነት ያለው አመራር ሰጪነት፣ ኢንቨስትመንትን ማጠናከር እና ተከታታይነት ያለው ውይይቶችን ማድረግ ይገባል። ውሳኔ ሰጪዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኙ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ መድረኮች በአጀንዳዎች ላይ የተቀናጀ የተግበባር ምላሽ ለመስጠት ቁልፍ ሚና አላቸው። አፍሪካ እድሎቿን በመጠቀም እና ፈተናዎቿን በማለፍ መንገድ ላይ በሆነችበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ ሁለት ወሳኝ አህጉራዊ ሁነቶችን ታስተናግዳለች። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የመሪዎች ጉባኤ መሪ ሀሳብ ነው።   ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። የመሪዎች ጉባኤው በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ያስተላልፋል ተብሎም ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ኮሚቴ ተወካዮች (PRC) ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ መክሯል።   ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን አቅርቧል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። ከአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ማግስት ሌላኛው በኢትዮጵያ የሚካሄደው ዘጠነኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ነው። የቢዝነስ ፎረሙ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(ኢሴኤ) ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሁነቱን አዘጋጅተውታል። “የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ በፋይናንስ መደገፍ፤ ስራ እና ኢኖቬሽን ለዘላቂ ትራንስፎርሜሽን” የፎረሙ መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም በአፍሪካ የልማት እና የኢኮኖሚ እድገት ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን በማድረግ በየዓመቱ የሚካሄድ ከፍተኛ አህጉራዊ የምክክር መድረክ መሆኑን የኢሲኤ መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ አጋርነትና የኢንቨስትመንት መጠንን ማሳደግ በተለይም የመንግስት እና የግል የተቀናጀ የፋይናንስ አቅርቦትን ጨምሮ የተለያዩ የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይወያያል። የወጣቶችን የኢኖቬሽን ስራ ከፋይናንስ አቅርቦት ጋር የሚያስተሳስር የአፍሪካ የወጣቶች አይበገሬነትና ትራንስፎርሜሽን ማዕቀፍ ይፋ ይሆናል። በኢሲኤ የበለጸገውና የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ ቃል ኪዳኖችን ትግበራ የሚከታታልና የሚቆጣጠር ስርዓትም በፎረሙ ይፋ ሆኖ ወደ ትግበራ ይገባል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው ሁነት ላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የምክክር መድረኮችና የባለሙያዎች ውይይቶች ይደረጋሉ።   አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጣራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ አውደ ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። ከአህጉራዊ ሁነቶቹ ባሻገር የባለብዙ ወገን መድረክ የሆነው የአፍሪካ እና ጣልያን ጉባኤ የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ሁነቶቹን ማዘጋጀቷ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ጸንቶ የቆየውን የመሪነት ሚናዋን እንዲሁም የአህጉራዊ ምክክር፣ የባለብዙ ወገን ውይይቶችና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባት ማዕከልነቷንም አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ በኮሪደር ልማት እና በከተማ ማዘመን ስራ በፍጥነት እየተለወጠች ሲሆን የሁነቱ ተሳታፊዎች ከስብሰባው ባለፈ የመዲናዋን አዲስ መልክ የመመልከት እድል ያገኛሉ። የእነዚህ አህጉራዊ ስብሰባዎች ስኬት የሚለካው በአቋም መግለጫ ሳይሆን አጋርነትን በማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና የሚጨበጥ ውጤት በአህጉሪቱ በማስመዝገብ ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ የምታዘጋጃቸው አህጉራዊ ሁነቶች አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጣራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ አውደ ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። ከአህጉራዊ ሁነቶቹ ባሻገር የባለብዙ ወገን መድረክ የሆነው የአፍሪካ እና ጣልያን ጉባኤ የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ሁነቶቹን ማዘጋጀቷ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ጸንቶ የቆየውን የመሪነት ሚናዋን እንዲሁም የአህጉራዊ ምክክር፣ የባለብዙ ወገን ውይይቶችና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባት ማዕከልነቷንም አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ በኮሪደር ልማት እና በከተማ ማዘመን ስራ በፍጥነት እየተለወጠች ሲሆን የሁነቱ ተሳታፊዎች ከስብሰባው ባለፈ የመዲናዋን አዲስ መልክ የመመልከት እድል ያገኛሉ። የእነዚህ አህጉራዊ ስብሰባዎች ስኬት የሚለካው በአቋም መግለጫ ሳይሆን አጋርነትን በማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና የሚጨበጥ ውጤት በአህጉሪቱ በማስመዝገብ ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ የምታዘጋጃቸው አህጉራዊ ሁነቶች አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች።
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የጋራ አጀንዳ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት አለበት
Feb 3, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የጋራ አጀንዳ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት እንዳለበት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀይ ባሕርን ጉዳይ በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፥ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለው ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ ጥረት እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና ቀይ ባህር ለዘለዓለም ተነጣጥለው እንደማይኖሩ በመግለጽ ፍትሐዊ ጥያቄያችን በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በድርድር መርህ ምላሽ እንዲያገኝ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ ፍትሐዊ ካልሆነ በዓለም ላይ ፍትሕ የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጊዜ ጉዳይ እንጂ መልስ ማግኘቱ አይቀሬ ነው ብለዋል፡፡   የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መስፍን እርካቤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ ምንም አይነት ልዩነት ሳይገድበን የጋራ አቋም ሊኖረን ይገባል ነው ያሉት፡፡ ብሔራዊ ጥቅም የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተው፤ የባህር በር ጉዳይን በሰላማዊ መንገድ ዕልባት እንዲያገኝ ማድረግ ግዴታ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ የበለጸገችና የተከበረች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የቀይ ባህር ጉዳይ በሁሉም ማህበረሰብ ዘንድ የጋራ መግባባት የተፈጠረበት አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የምክር ቤት አባል ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ የምታነሳው ጥያቄ ፍትሕን የማረጋገጥ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት ከቀይ ባህር ባለቤትነት የራቀችው በወቅቱ በነበረው መንግሥት ቸልተኝነት መሆኑን በመጥቀስ፤ እያደገ ያለ ኢኮኖሚ ይዛ የባህር በር ሊዘጋባት እንደማይገባ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲና የመደራደር አቅም እያደገ መምጣቱን በመግለጽ፤ ጥያቄያችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ምላሽ ሊያገኝ ይገባል ብለዋል፡፡   ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያን ቀይ ባህር የብሔራዊ ጥቅማችን አጀንዳ በመሆኑ በጋራ መስራት አለብን ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚያሳዩ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች እያደረገች መሆኑን በማንሳት፤ እኛም የፖለቲካ ልዩነትን ወደ ጎን በመተው በጋራ እየሠራን ነው ብለዋል፡፡ በመንግሥት በኩል እየተከናወኑ ያሉ በሳል የውጭ ግንኙነት ስራዎች ኢትዮጵያን በቀጣናው ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች የተሻለ ሆና መውጣት ያስችሏታል ሲሉም ተናግረዋል፡፡    

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ለማድረግ ቁርጠኝነቱን አሳይቷል
Feb 4, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ለማድረግ ቁርጠኝነቱን አሳይቷል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም የዘንድሮው ምርጫ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊ፣ አካታች እና ካለፈው ምርጫ የተሻለ እንዲሆን እንፈልጋለን ብለዋል፡፡ መንግሥት የምርጫ አውዱን ለማስፋት በተለየ ትኩረት እየሠራ መሆኑን ጠቁመው በዚህም አሁን ካለው እስከ 10 እጥፍ የሚሆኑ ልዩ ድምፆች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይገኛሉ ሲሉም ገልጸዋል። የዘንድሮውን ምርጫ ተዓማኒ ካለፈው የተሻለ አሳታፊ እና አካታች ለማድረግ ምቹ ከባቢ መፍጠር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) መንግሥት ከምርጫው ዝግጅትና ዲሞክራሲያዊነት አንፃር ለቀረበለት ጥያቄ አጥጋቢ ምላሽ ሰጥቷል ብለዋል፡፡ መንግሥት 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ እና አሳታፊ ለማድረግ ቁርጠኝነቱን ማሳየቱን ገልጸዋል፡፡   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መስፍን እርካቤ፤ ምርጫውን ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ማከናወን የሚያስችል አውድ መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ በሕልውና ዘመቻ ላይ በነበረችበት ወቅትም ምርጫ ማካሄዷን አስታውሰው፤ የዘንድሮውን ምርጫ ሊያስተጓጉል የሚችል የሰላም እጦት የለም ነው ያሉት፡፡ ምርጫው ፍትሐዊ ዲሞክራሲያዊና በሕዝቡ ዘንድ ተዓማኒ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸው፤ ለዚህም ፓርቲዎች የእጩዎች ምዝገባ መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ምክር ቤት አባል ዑስታዝ ካሚል ሸምሱ፤ ምርጫ የአንድ ማኅበረሰብ የዲሞክራሲ ልምምድ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ምርጫውን ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ለማከናወን ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ ባሻገር ደግሞ ማኅበረሰቡ ምርጫው አሳታፊ እንዲሆን ሚናውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ተግባራዊ ሊያደርግ ነው
Feb 4, 2026 71
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልገሎት መስጠት የሚያስችል የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ማድረጉን አስታወቀ።   የሰሌዳ ለውጡ ከነገ ጥር 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆንም ተገልጿል። በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የሎጂስቲክስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር እሸቱ ፊጣ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጡን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን ማብራሪያ ሰጥተዋል። የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጡ ተቋሙ እያከናወነ ያለው ሁሉን አቀፍ የሪፎርም ሥራ አካል ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር እንዲኖራቸው ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል። ቀደም ሲል አገልግሎት ላይ የቆየው ሰሌዳ ወጥነት የሌለው እና የተዘበራረቀ በመሆኑ ለአሠራር አስቸጋሪ ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል። ተቋሙ ዘመኑን የሚመጥን ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰረ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ማድረጉን ጠቅሰዋል፡፡   የሰሌዳ ለውጡ ለዜጎች የሚሰጠውን አገልግሎት ፈጣን፣ ዘመናዊና ግልጽ በማድረግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ነው ያሉት። በተጨማሪም የተቋሙን ተሽከርካሪ በመጠቀም የሚፈጸም የስነ-ምግባርና መሰል ጥሰቶችን በተሟላ መልኩ ለመከላከልና ለመቆጣጠር አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥር አረጋግጠዋል። ከነገ ጀምሮ በይፋ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ከዲጂታል የመረጃ ቋት ጋር የተሳሰረ መሆኑ ለአሠራርና ለቁጥጥር መጠናከር እንዲሁም ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አይነተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። አዳዲሶቹ ሰሌዳዎች በህገ-ወጥ መንገድ የማይባዙና የደህንነት መጠበቂያ ሚስጥራዊ መለያ ያላቸው በመሆናቸው ለየትኛውም የማጭበርበር ወንጀል ተጋላጭ እንደማይሆኑ ገልጸዋል። ይህም የተቋሙን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚጨምርና አገልግሎቱን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ስለመሆኑ በማብራሪያቸው አንስተዋል።  
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ተዘጋጅተናል - የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት
Feb 4, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ሰፊ ዝግጅት ማድረጉን የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት አስታወቀ። የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አሕመድ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በቀጣይ የሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን ምክር ቤቱ ሰፊ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤ፣ የፓርቲዎች ክርክርና የግልጽነት መድረኮች ማመቻቸት እንዲሁም የምርጫ ታዛቢነት ሥራቸውን ለመወጣት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር በቅንጅት እየሠሩ መሆኑን ተናግረዋል። ከ200 በላይ የሲቪክ ማኅበራት በምርጫ ቦርድ ተመዝግበው ፈቃድ መውሰዳቸውን ጠቁመው፤ ተቋማቱ ወደ ሥራ መግባት የሚያስችላቸውን ምስክር ወረቀት ከምርጫ ቦርድ እንዳገኙ በይፋ ተግባራቸውን ይጀምራሉ ብለዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ አዲስ አዋጅ መውጣቱንና ምቹ አሠራሮች መዘርጋታቸውን አስታውሰው፤ ይህም የሲቪክ ማኅበራት በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ማሳደጉን ፕሬዝዳንቱ አውስተዋል። ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሀገርን ለማሻገር፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍና ስልጡን የፖለቲካ ባህልን ለማሳደግ ወሳኝ መሣሪያ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ይጠቅመኛል የሚሉትን መንግሥት በሰላማዊ መንገድ በድምፃቸው እንዲመርጡ ሰፊ የምርጫ ትምህርት ለመስጠት መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል፡፡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሐሳባቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት መድረክ በማመቻቸት፣ መራጮች የሚበጃቸውን አካል በዕውቀት ላይ ተመስርተው እንዲመርጡ እንደሚሰሩም ገልጸዋል። በሌላ መልኩ የምርጫውን ሂደት ታማኝነት ለማረጋገጥ የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶቹ በታዛቢነት በመሳተፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ጠቅሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የጋራ አጀንዳ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት አለበት
Feb 3, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የጋራ አጀንዳ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት እንዳለበት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀይ ባሕርን ጉዳይ በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፥ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለው ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ ጥረት እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና ቀይ ባህር ለዘለዓለም ተነጣጥለው እንደማይኖሩ በመግለጽ ፍትሐዊ ጥያቄያችን በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በድርድር መርህ ምላሽ እንዲያገኝ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ ፍትሐዊ ካልሆነ በዓለም ላይ ፍትሕ የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጊዜ ጉዳይ እንጂ መልስ ማግኘቱ አይቀሬ ነው ብለዋል፡፡   የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መስፍን እርካቤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ ምንም አይነት ልዩነት ሳይገድበን የጋራ አቋም ሊኖረን ይገባል ነው ያሉት፡፡ ብሔራዊ ጥቅም የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተው፤ የባህር በር ጉዳይን በሰላማዊ መንገድ ዕልባት እንዲያገኝ ማድረግ ግዴታ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ የበለጸገችና የተከበረች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የቀይ ባህር ጉዳይ በሁሉም ማህበረሰብ ዘንድ የጋራ መግባባት የተፈጠረበት አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የምክር ቤት አባል ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ የምታነሳው ጥያቄ ፍትሕን የማረጋገጥ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት ከቀይ ባህር ባለቤትነት የራቀችው በወቅቱ በነበረው መንግሥት ቸልተኝነት መሆኑን በመጥቀስ፤ እያደገ ያለ ኢኮኖሚ ይዛ የባህር በር ሊዘጋባት እንደማይገባ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲና የመደራደር አቅም እያደገ መምጣቱን በመግለጽ፤ ጥያቄያችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ምላሽ ሊያገኝ ይገባል ብለዋል፡፡   ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያን ቀይ ባህር የብሔራዊ ጥቅማችን አጀንዳ በመሆኑ በጋራ መስራት አለብን ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚያሳዩ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች እያደረገች መሆኑን በማንሳት፤ እኛም የፖለቲካ ልዩነትን ወደ ጎን በመተው በጋራ እየሠራን ነው ብለዋል፡፡ በመንግሥት በኩል እየተከናወኑ ያሉ በሳል የውጭ ግንኙነት ስራዎች ኢትዮጵያን በቀጣናው ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች የተሻለ ሆና መውጣት ያስችሏታል ሲሉም ተናግረዋል፡፡    
በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመፎካከር ዝግጅት እያደረኩ ነው - ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
Feb 3, 2026 130
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመፎካከር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አስታወቀ። ፓርቲው ለመጪው ምርጫ የሚመራበትን ፍኖተ ካርታ የያዘ ስትራቴጂ ሰነድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። የስትራቴጂ ሰነዱ በያዛቸው አንኳር ጉዳዮችና አተገባበር ዙሪያ የፓርቲው አመራር አባላት ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።   የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሊቀ መንበር ዶክተር አብዱልቃድር አደም እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ልምምድ እንዲዳብር ፓርቲው የበኩሉን ገንቢ ሚና እየተጫወተ ነው። ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲካሄድ ፓርቲው ከወዲሁ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ ቀጣይ ተግባራቱ ፓርቲው ባዘጋጀው የምርጫ ስትራቴጂ ሰነድ ውስጥ መካተቱን አስረድተዋል። ፓርቲው የምርጫ ተሳትፎ የሥነ ምግባር መመሪያ ማዘጋጀቱን የገለጹት ሊቀ መንበሩ፤ መርህን የተከተለ የፖለቲካ ክርክር ለማድረግም ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል። የፓርቲው ዕጩዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች በቀጣዩ ምርጫ ገንቢ ሚና መጫወት የሚያስችላቸውን ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።   የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የምርጫ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ካሚል ሰኢድ በበኩላቸው፤ ፓርቲው በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ መቀጠሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የምትሻገረው የሕዝብና የአገር ጥቅምን ማስቀደም ሲቻል ነው ያሉት ኃላፊው፤ ፓርቲው በሀገራዊ ጉዳይ ላይ መንግሥትን ጨምሮ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በሀገራዊ ምክክሩ ላይም ፓርቲው የጀመረውን ተሳትፎ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።   የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ ነቢሀ መሀመድ እንዳሉት፤ ፓርቲው በመጪው ምርጫ 1ሺ 500 ዕጩዎችን ለማቅረብ እየሰራ ነው። በምርጫው ላይ ውጤታማ በሆኑ መልኩ ለመሳተፍ ዛሬ ይፋ ያደረገው ስትራቴጂ ትልቅ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው፤ የፓርቲው አባላት፣ ደጋፊዎችና ዕጩዎች ሚናቸውን በላቀ ደረጃ እንዲወጡ በስትራቴጂው ዙሪያ ግንዛቤ የሚያስጨብጡ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።   የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሲሳይ ነጋሽ በበኩላቸው፤ የምርጫ ስትራቴጂው ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች፣ መገናኛ ብዙኃን ጨምሮ ከባላድርሻ አካላት ጋር በትብብር መሥራት የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ያመላከተ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ እና ቀይ ባህር ለዘላለም ተነጣጥለው መኖር አይችሉም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Feb 3, 2026 210
አዲስ አበባ፤ ጥር 26 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቀይ ባህር ለዘላለም ተነጣጥለው መኖር አይችሉም፣ ቀይ ባህር የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ቀንድ እንዳይቀደድ የተሰፋ እንዳይጣመር የተቀፈደደ ነው ሲሉ በቀጣናው ያለውን ጂኦ ፖለቲካዊ ሁኔታ ገልጸዋል። የቀጣናው ማህበረሰብ በባህል፣ ታሪክ እና በቋንቋ የተሳሰረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይሁንና ቀጣናው በከፍተኛ ፉክክር እና ጣልቃ ገብነት የተከበበ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር አይገባትም ብሎ የሚያምን ሰው ተፈጥሯዊ ህግ መሳቱንም አመልክተዋል። ቀይ ባህር እና ኢትዮጵያ ለዘላለም ተነጣጥለው መኖር እንደማይችሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጉዳይ በሰላማዊ መንገድ፤ በስምምነት እና በገበያ ህግ በድርድር እንፍታ የሚል ጽኑ አቋም እንዳላት አመልክተዋል። ቀይ ባህርን ዛሬ ላይ ለመከልከል ቢሞክር አካሄዱ አግባብ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን ከተፈጥሯዊ ጸጋ ማስቀረት እንደማይቻል ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ጉዳዩን በሰላም እና በድርድር ብቻ የመፍታት ጽኑ አቋም እንዳላትም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጉዳይ መቼም ሊቆም እና ሊቀር የማይችል የህልውና ጉዳይ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ያለንን ሀብት በጋራ በመጠቀም በጋራ እንልማ ሲሉም ለጎረቤት ሀገራት መልዕክት አስተላልፈዋል።
የአፍሪካ ቀንድ እንዳይቀደድ የተሰፋ፤ እንዳይጣመር የተቀፈደደ ከባቢ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Feb 3, 2026 140
አዲስ አበባ፤ጥር 26 /2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ቀንድ እንዳይቀደድ የተሰፋ፤ እንዳይጣመር የተቀፈደደ ከባቢ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የአፍሪካ ቀንድ ከባቢን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ የአፍሪካ ቀንድ እንዳይቀደድ የተሰፋ፤ እንዳይጣመር የተቀፈደደ ከባቢ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፥ በባህልና ቀንቋ የሚተሳሰሩ ህዝቦች ያሉበት ቢሆንም ከፍተኛ ፉክክርና ጣልቃ ገብነት ያለው ከባቢ ነው ያሉት። የሁለቱ ውሃዎች ጉዳይ እኛንም እያተረማመሰ በእኛ ጉዳይ የሚገቡ ሃይሎችን እያሰፋ አንዱ ለአንዱ መከታ ሊሆን ሲገባው ችግር አስተላላፊ መሆኑን ገልጸው፥ በዚህ ምክንያት ቀጠናው የራሱ ችግር ያለበት በመሆኑ ይህን ለማስፋት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፤እንደሚሳካም እምነት አለኝ ሲሉ ተናግረዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሚያስችል መደላድል መፍጠር ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Feb 3, 2026 111
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018 (ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሚያስችል መደላድል መፍጠር እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም ምክክር ልብን ያሳርፋል፤ በውይይት በርካታ ስብራቶች ይጠገናሉ ብለዋል፡፡ አሁን ያለው ትውልድ በውይይት ሀገር መሥራት እንዳለበት ተናግረው፣ ለመወያየት ዝግጁ መሆን እንደሚገባም ነው የገለጹት፡፡ ኮሚሽኑ እስካሁን በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ማወያየቱን ጠቅሰው፤ በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአፍሪካ እና በሁሉም አካባቢዎች ያሉ ኢትዮጵያውያንን ተደራሽ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በርካታ አጀንዳዎችን መሰብሰቡን ገልጸው፣ እስካሁን የአጀንዳ ማሰባሰብና ለዋናው መድረክ የሚወያዩ ሰዎችን የመለየት ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል፡፡ በትግራይ ክልልም ከአሥር በላይ ስብሰባዎች መደረጋቸውን ጠቁመው፣ በአጠቃላይ ከ95 በመቶ በላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ውክልና ማግኘቱንም ገልጸዋል፡፡ ምክክሩን ሊያቆም የሚችል ምንም ዓይነት ነገር አለመኖሩንም አረጋግጠዋል፡፡ የምክክሩን አካታችነት አስመልክተውም፣ አልፈልግም የሚል አካል ካለ እንደማይገደድ ነው የተናገሩት፡፡ ስለ ምክክሩ ጠቀሜታ ለሁሉም የማስገንዘብ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ብዙኃኑ የተስማሙበት ሐሳብ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በተሰበሰቡ አጀንዳዎች ላይ በሳል ውይይት በማድረግ ለልጆቻችን ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሚያስችል መደላድል መፍጠር ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ የኮሚሽኑ ቀጣይ ሥራ ለዋናው ጉባኤ የተመረጡ ሰዎችን አወያይቶ፣ አጀንዳውን አብላልቶ፣ ለምክር ቤቱ እና ለመንግሥት የሚሆን ድምዳሜ ማውጣት እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ እስካሁን ያለው ሂደት እጅግ ተስፋ ሰጪና ትምህርት የተገኘበት መሆኑን ገልጸው፤ ለአብነትም በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ አርሶ አደሮች ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳላቸው በተግባር መረጋገጡን ለምክር ቤቱ አብራርተዋል፡፡
ፖለቲካ
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ለማድረግ ቁርጠኝነቱን አሳይቷል
Feb 4, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ለማድረግ ቁርጠኝነቱን አሳይቷል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም የዘንድሮው ምርጫ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊ፣ አካታች እና ካለፈው ምርጫ የተሻለ እንዲሆን እንፈልጋለን ብለዋል፡፡ መንግሥት የምርጫ አውዱን ለማስፋት በተለየ ትኩረት እየሠራ መሆኑን ጠቁመው በዚህም አሁን ካለው እስከ 10 እጥፍ የሚሆኑ ልዩ ድምፆች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይገኛሉ ሲሉም ገልጸዋል። የዘንድሮውን ምርጫ ተዓማኒ ካለፈው የተሻለ አሳታፊ እና አካታች ለማድረግ ምቹ ከባቢ መፍጠር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) መንግሥት ከምርጫው ዝግጅትና ዲሞክራሲያዊነት አንፃር ለቀረበለት ጥያቄ አጥጋቢ ምላሽ ሰጥቷል ብለዋል፡፡ መንግሥት 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ እና አሳታፊ ለማድረግ ቁርጠኝነቱን ማሳየቱን ገልጸዋል፡፡   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መስፍን እርካቤ፤ ምርጫውን ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ማከናወን የሚያስችል አውድ መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ በሕልውና ዘመቻ ላይ በነበረችበት ወቅትም ምርጫ ማካሄዷን አስታውሰው፤ የዘንድሮውን ምርጫ ሊያስተጓጉል የሚችል የሰላም እጦት የለም ነው ያሉት፡፡ ምርጫው ፍትሐዊ ዲሞክራሲያዊና በሕዝቡ ዘንድ ተዓማኒ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸው፤ ለዚህም ፓርቲዎች የእጩዎች ምዝገባ መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ምክር ቤት አባል ዑስታዝ ካሚል ሸምሱ፤ ምርጫ የአንድ ማኅበረሰብ የዲሞክራሲ ልምምድ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ምርጫውን ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ለማከናወን ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ ባሻገር ደግሞ ማኅበረሰቡ ምርጫው አሳታፊ እንዲሆን ሚናውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ተግባራዊ ሊያደርግ ነው
Feb 4, 2026 71
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልገሎት መስጠት የሚያስችል የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ማድረጉን አስታወቀ።   የሰሌዳ ለውጡ ከነገ ጥር 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆንም ተገልጿል። በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የሎጂስቲክስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር እሸቱ ፊጣ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጡን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን ማብራሪያ ሰጥተዋል። የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጡ ተቋሙ እያከናወነ ያለው ሁሉን አቀፍ የሪፎርም ሥራ አካል ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር እንዲኖራቸው ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል። ቀደም ሲል አገልግሎት ላይ የቆየው ሰሌዳ ወጥነት የሌለው እና የተዘበራረቀ በመሆኑ ለአሠራር አስቸጋሪ ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል። ተቋሙ ዘመኑን የሚመጥን ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰረ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ማድረጉን ጠቅሰዋል፡፡   የሰሌዳ ለውጡ ለዜጎች የሚሰጠውን አገልግሎት ፈጣን፣ ዘመናዊና ግልጽ በማድረግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ነው ያሉት። በተጨማሪም የተቋሙን ተሽከርካሪ በመጠቀም የሚፈጸም የስነ-ምግባርና መሰል ጥሰቶችን በተሟላ መልኩ ለመከላከልና ለመቆጣጠር አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥር አረጋግጠዋል። ከነገ ጀምሮ በይፋ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ከዲጂታል የመረጃ ቋት ጋር የተሳሰረ መሆኑ ለአሠራርና ለቁጥጥር መጠናከር እንዲሁም ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አይነተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። አዳዲሶቹ ሰሌዳዎች በህገ-ወጥ መንገድ የማይባዙና የደህንነት መጠበቂያ ሚስጥራዊ መለያ ያላቸው በመሆናቸው ለየትኛውም የማጭበርበር ወንጀል ተጋላጭ እንደማይሆኑ ገልጸዋል። ይህም የተቋሙን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚጨምርና አገልግሎቱን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ስለመሆኑ በማብራሪያቸው አንስተዋል።  
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ተዘጋጅተናል - የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት
Feb 4, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን አዎንታዊ ሚና ለመወጣት ሰፊ ዝግጅት ማድረጉን የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት አስታወቀ። የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አሕመድ ሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በቀጣይ የሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን ምክር ቤቱ ሰፊ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤ፣ የፓርቲዎች ክርክርና የግልጽነት መድረኮች ማመቻቸት እንዲሁም የምርጫ ታዛቢነት ሥራቸውን ለመወጣት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር በቅንጅት እየሠሩ መሆኑን ተናግረዋል። ከ200 በላይ የሲቪክ ማኅበራት በምርጫ ቦርድ ተመዝግበው ፈቃድ መውሰዳቸውን ጠቁመው፤ ተቋማቱ ወደ ሥራ መግባት የሚያስችላቸውን ምስክር ወረቀት ከምርጫ ቦርድ እንዳገኙ በይፋ ተግባራቸውን ይጀምራሉ ብለዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ አዲስ አዋጅ መውጣቱንና ምቹ አሠራሮች መዘርጋታቸውን አስታውሰው፤ ይህም የሲቪክ ማኅበራት በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ማሳደጉን ፕሬዝዳንቱ አውስተዋል። ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሀገርን ለማሻገር፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍና ስልጡን የፖለቲካ ባህልን ለማሳደግ ወሳኝ መሣሪያ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ይጠቅመኛል የሚሉትን መንግሥት በሰላማዊ መንገድ በድምፃቸው እንዲመርጡ ሰፊ የምርጫ ትምህርት ለመስጠት መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል፡፡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሐሳባቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት መድረክ በማመቻቸት፣ መራጮች የሚበጃቸውን አካል በዕውቀት ላይ ተመስርተው እንዲመርጡ እንደሚሰሩም ገልጸዋል። በሌላ መልኩ የምርጫውን ሂደት ታማኝነት ለማረጋገጥ የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶቹ በታዛቢነት በመሳተፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ጠቅሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የጋራ አጀንዳ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት አለበት
Feb 3, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የጋራ አጀንዳ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት እንዳለበት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀይ ባሕርን ጉዳይ በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፥ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለው ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ ጥረት እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና ቀይ ባህር ለዘለዓለም ተነጣጥለው እንደማይኖሩ በመግለጽ ፍትሐዊ ጥያቄያችን በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በድርድር መርህ ምላሽ እንዲያገኝ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ ፍትሐዊ ካልሆነ በዓለም ላይ ፍትሕ የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጊዜ ጉዳይ እንጂ መልስ ማግኘቱ አይቀሬ ነው ብለዋል፡፡   የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መስፍን እርካቤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ ምንም አይነት ልዩነት ሳይገድበን የጋራ አቋም ሊኖረን ይገባል ነው ያሉት፡፡ ብሔራዊ ጥቅም የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተው፤ የባህር በር ጉዳይን በሰላማዊ መንገድ ዕልባት እንዲያገኝ ማድረግ ግዴታ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ የበለጸገችና የተከበረች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የቀይ ባህር ጉዳይ በሁሉም ማህበረሰብ ዘንድ የጋራ መግባባት የተፈጠረበት አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የምክር ቤት አባል ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ የምታነሳው ጥያቄ ፍትሕን የማረጋገጥ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት ከቀይ ባህር ባለቤትነት የራቀችው በወቅቱ በነበረው መንግሥት ቸልተኝነት መሆኑን በመጥቀስ፤ እያደገ ያለ ኢኮኖሚ ይዛ የባህር በር ሊዘጋባት እንደማይገባ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲና የመደራደር አቅም እያደገ መምጣቱን በመግለጽ፤ ጥያቄያችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ምላሽ ሊያገኝ ይገባል ብለዋል፡፡   ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያን ቀይ ባህር የብሔራዊ ጥቅማችን አጀንዳ በመሆኑ በጋራ መስራት አለብን ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚያሳዩ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች እያደረገች መሆኑን በማንሳት፤ እኛም የፖለቲካ ልዩነትን ወደ ጎን በመተው በጋራ እየሠራን ነው ብለዋል፡፡ በመንግሥት በኩል እየተከናወኑ ያሉ በሳል የውጭ ግንኙነት ስራዎች ኢትዮጵያን በቀጣናው ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች የተሻለ ሆና መውጣት ያስችሏታል ሲሉም ተናግረዋል፡፡    
በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመፎካከር ዝግጅት እያደረኩ ነው - ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
Feb 3, 2026 130
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመፎካከር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አስታወቀ። ፓርቲው ለመጪው ምርጫ የሚመራበትን ፍኖተ ካርታ የያዘ ስትራቴጂ ሰነድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። የስትራቴጂ ሰነዱ በያዛቸው አንኳር ጉዳዮችና አተገባበር ዙሪያ የፓርቲው አመራር አባላት ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።   የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሊቀ መንበር ዶክተር አብዱልቃድር አደም እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ልምምድ እንዲዳብር ፓርቲው የበኩሉን ገንቢ ሚና እየተጫወተ ነው። ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲካሄድ ፓርቲው ከወዲሁ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ ቀጣይ ተግባራቱ ፓርቲው ባዘጋጀው የምርጫ ስትራቴጂ ሰነድ ውስጥ መካተቱን አስረድተዋል። ፓርቲው የምርጫ ተሳትፎ የሥነ ምግባር መመሪያ ማዘጋጀቱን የገለጹት ሊቀ መንበሩ፤ መርህን የተከተለ የፖለቲካ ክርክር ለማድረግም ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል። የፓርቲው ዕጩዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች በቀጣዩ ምርጫ ገንቢ ሚና መጫወት የሚያስችላቸውን ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።   የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የምርጫ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ካሚል ሰኢድ በበኩላቸው፤ ፓርቲው በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ መቀጠሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የምትሻገረው የሕዝብና የአገር ጥቅምን ማስቀደም ሲቻል ነው ያሉት ኃላፊው፤ ፓርቲው በሀገራዊ ጉዳይ ላይ መንግሥትን ጨምሮ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በሀገራዊ ምክክሩ ላይም ፓርቲው የጀመረውን ተሳትፎ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።   የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ ነቢሀ መሀመድ እንዳሉት፤ ፓርቲው በመጪው ምርጫ 1ሺ 500 ዕጩዎችን ለማቅረብ እየሰራ ነው። በምርጫው ላይ ውጤታማ በሆኑ መልኩ ለመሳተፍ ዛሬ ይፋ ያደረገው ስትራቴጂ ትልቅ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው፤ የፓርቲው አባላት፣ ደጋፊዎችና ዕጩዎች ሚናቸውን በላቀ ደረጃ እንዲወጡ በስትራቴጂው ዙሪያ ግንዛቤ የሚያስጨብጡ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።   የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሲሳይ ነጋሽ በበኩላቸው፤ የምርጫ ስትራቴጂው ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች፣ መገናኛ ብዙኃን ጨምሮ ከባላድርሻ አካላት ጋር በትብብር መሥራት የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ያመላከተ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ እና ቀይ ባህር ለዘላለም ተነጣጥለው መኖር አይችሉም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Feb 3, 2026 210
አዲስ አበባ፤ ጥር 26 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቀይ ባህር ለዘላለም ተነጣጥለው መኖር አይችሉም፣ ቀይ ባህር የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ቀንድ እንዳይቀደድ የተሰፋ እንዳይጣመር የተቀፈደደ ነው ሲሉ በቀጣናው ያለውን ጂኦ ፖለቲካዊ ሁኔታ ገልጸዋል። የቀጣናው ማህበረሰብ በባህል፣ ታሪክ እና በቋንቋ የተሳሰረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይሁንና ቀጣናው በከፍተኛ ፉክክር እና ጣልቃ ገብነት የተከበበ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር አይገባትም ብሎ የሚያምን ሰው ተፈጥሯዊ ህግ መሳቱንም አመልክተዋል። ቀይ ባህር እና ኢትዮጵያ ለዘላለም ተነጣጥለው መኖር እንደማይችሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጉዳይ በሰላማዊ መንገድ፤ በስምምነት እና በገበያ ህግ በድርድር እንፍታ የሚል ጽኑ አቋም እንዳላት አመልክተዋል። ቀይ ባህርን ዛሬ ላይ ለመከልከል ቢሞክር አካሄዱ አግባብ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን ከተፈጥሯዊ ጸጋ ማስቀረት እንደማይቻል ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ጉዳዩን በሰላም እና በድርድር ብቻ የመፍታት ጽኑ አቋም እንዳላትም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጉዳይ መቼም ሊቆም እና ሊቀር የማይችል የህልውና ጉዳይ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ያለንን ሀብት በጋራ በመጠቀም በጋራ እንልማ ሲሉም ለጎረቤት ሀገራት መልዕክት አስተላልፈዋል።
የአፍሪካ ቀንድ እንዳይቀደድ የተሰፋ፤ እንዳይጣመር የተቀፈደደ ከባቢ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Feb 3, 2026 140
አዲስ አበባ፤ጥር 26 /2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ቀንድ እንዳይቀደድ የተሰፋ፤ እንዳይጣመር የተቀፈደደ ከባቢ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የአፍሪካ ቀንድ ከባቢን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ የአፍሪካ ቀንድ እንዳይቀደድ የተሰፋ፤ እንዳይጣመር የተቀፈደደ ከባቢ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፥ በባህልና ቀንቋ የሚተሳሰሩ ህዝቦች ያሉበት ቢሆንም ከፍተኛ ፉክክርና ጣልቃ ገብነት ያለው ከባቢ ነው ያሉት። የሁለቱ ውሃዎች ጉዳይ እኛንም እያተረማመሰ በእኛ ጉዳይ የሚገቡ ሃይሎችን እያሰፋ አንዱ ለአንዱ መከታ ሊሆን ሲገባው ችግር አስተላላፊ መሆኑን ገልጸው፥ በዚህ ምክንያት ቀጠናው የራሱ ችግር ያለበት በመሆኑ ይህን ለማስፋት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፤እንደሚሳካም እምነት አለኝ ሲሉ ተናግረዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሚያስችል መደላድል መፍጠር ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Feb 3, 2026 111
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018 (ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሚያስችል መደላድል መፍጠር እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም ምክክር ልብን ያሳርፋል፤ በውይይት በርካታ ስብራቶች ይጠገናሉ ብለዋል፡፡ አሁን ያለው ትውልድ በውይይት ሀገር መሥራት እንዳለበት ተናግረው፣ ለመወያየት ዝግጁ መሆን እንደሚገባም ነው የገለጹት፡፡ ኮሚሽኑ እስካሁን በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ማወያየቱን ጠቅሰው፤ በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአፍሪካ እና በሁሉም አካባቢዎች ያሉ ኢትዮጵያውያንን ተደራሽ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በርካታ አጀንዳዎችን መሰብሰቡን ገልጸው፣ እስካሁን የአጀንዳ ማሰባሰብና ለዋናው መድረክ የሚወያዩ ሰዎችን የመለየት ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል፡፡ በትግራይ ክልልም ከአሥር በላይ ስብሰባዎች መደረጋቸውን ጠቁመው፣ በአጠቃላይ ከ95 በመቶ በላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ውክልና ማግኘቱንም ገልጸዋል፡፡ ምክክሩን ሊያቆም የሚችል ምንም ዓይነት ነገር አለመኖሩንም አረጋግጠዋል፡፡ የምክክሩን አካታችነት አስመልክተውም፣ አልፈልግም የሚል አካል ካለ እንደማይገደድ ነው የተናገሩት፡፡ ስለ ምክክሩ ጠቀሜታ ለሁሉም የማስገንዘብ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ብዙኃኑ የተስማሙበት ሐሳብ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በተሰበሰቡ አጀንዳዎች ላይ በሳል ውይይት በማድረግ ለልጆቻችን ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሚያስችል መደላድል መፍጠር ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ የኮሚሽኑ ቀጣይ ሥራ ለዋናው ጉባኤ የተመረጡ ሰዎችን አወያይቶ፣ አጀንዳውን አብላልቶ፣ ለምክር ቤቱ እና ለመንግሥት የሚሆን ድምዳሜ ማውጣት እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ እስካሁን ያለው ሂደት እጅግ ተስፋ ሰጪና ትምህርት የተገኘበት መሆኑን ገልጸው፤ ለአብነትም በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ አርሶ አደሮች ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳላቸው በተግባር መረጋገጡን ለምክር ቤቱ አብራርተዋል፡፡
ማህበራዊ
መምህራን ለትውልድ ግንባታ ያላቸው አበርክቶ በመንግስትና በሕዝብ ዘንድ ትልቅ ክብር የሚሰጠው ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Feb 4, 2026 20
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፡- መምህራን ለሀገርና ለትውልድ ግንባታ ያላቸው አበርክቶ በመንግስትና በሕዝብ ዘንድ ትልቅ ክብር የሚሰጠው መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ የሚገኙ መምህራን የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን የመምህራን የመኖሪያ መንደር ግንባታ በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል።   በዚህም በ57 ማኅበራት የተደራጁ 6 ሺህ 194 መምህራንን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሲሆን፤ ተጠቃሚዎቹ የቤቱን ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ አስቀድመው የቆጠቡ ናቸው። ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ለመኖር ምቹ እና ለጎብኚዎች ሳቢ እየሆነች መጥታለች። ይህንን ዕድገት ተከትሎ የሚመጣውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ አማራጮች የቤት ግንባታዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በርካታ ቤቶች ተገንብተው ለተጠቃሚዎች ማስተላለፍ ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ ዛሬ ደግሞ የሀገር ግንባታ ምሰሶ ለሆኑት መምህራን ልዩ ትኩረት በመስጠት ይህን ግንባታ ጀምረናል ብለዋል። በማህበር ቤት ግንባታ መምህራን ፋና ወጊዎች ናቸው ያሉት ከንቲባዋ መምህራኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ 4 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ በመቆጠብ አስደናቂ ውጤት አስመዝግበዋል ነው ያሉት።   አስተዳደሩ ለመጀመሪያው ዙር የሚውል 40 ሄክታር መሬት ለመምህራኑ ያዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው መምህራን ሀገርን ለመገንባት ለሚከፍሉት ዋጋ በመንግስትና በህዝብ ዘንድ ያለውን ክብር በተግባር ያሳየንበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ትምሀርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዛሬው ዕለት በ57 ማህበራት የተደራጁ 6ሺህ 194 መምህራን የግንባታ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ መምህራን የትውልድ ቀራጭ፣ የሀገር ግንባታና የብልፅግና መሰረት በመሆናቸው ለሙያው የሚገባውን ክብር ለመስጠት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።   የመምህራንን የቤት ችግር በዘላቂነት መፍታት ሙሉ ትኩረታቸውን በትምህርት ጥራትና በትውልድ ግንባታ ላይ እንዲያደርጉ ማስቻል ነው ብለዋል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ ቤቶቹ በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ተገንብተው ለተጠቃሚዎች እንዲቀርቡ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ፤ አስተዳደሩ ለመምህራን ትኩረት በመስጠት የቤት ጥያቄያቸውን የሚመልሥ ተጨባጭ ተግባር እያከናወነ በመሆኑ ምስጋናቸውን ገልጸዋል። ይህ ምላሽ በመምህራን ዘንድ ለዓመታት የቆየውን የኑሮ ጫና የሚቀንስና በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ የተሻለ መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን የሰጡ መምህር እንዳልካቸው ደጀኔ፣ መምህር መስከረም ጎቤና እና መምህር ደለለኝ አስማሬ መምህራኑ ለረጅም ጊዜ ሲያቀርቡት የነበረው የቤት ጥያቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአስተዳደሩ ምላሽ በማግኘቱ አመስግነዋል።
አስተዳደሩ የመዲናዋን የቤት አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ልዩ ልዩ የቤት ግንባታ አማራጮችን ተግባራዊ ማድረጉን አጠናክሮ ይቀጥላል
Feb 4, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት አቅርቦት ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ልዩ ልዩ አማራጮችን ተግባራዊ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ የሚገኙ መምህራን የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን የመምህራን የመኖሪያ መንደር ግንባታ በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል።   በዚህም በ57 ማኅበራት የተደራጁ 6ሺህ 194 መምህራንን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሲሆን፤ ተጠቃሚዎቹ የቤቱን ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ አስቀድመው የቆጠቡ ናቸው። ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ለመኖር ምቹ እና ለጎብኚዎች ሳቢ እየሆነች መጥታለች።   ይህንን ዕድገት ተከትሎ የሚመጣውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ አማራጮች የቤት ግንባታዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በርካታ ቤቶች ተገንብተው ለተጠቃሚዎች ማስተላለፍ ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ ዛሬ ደግሞ የሀገር ግንባታ ምሰሶ ለሆኑት መምህራን ልዩ ትኩረት በመስጠት ይህን ግንባታ ጀምረናል ነው ያሉት። መምህራን በማኅበር ተደራጅተውና ተገቢውን ቁጠባ በማድረግ የዕድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም ተናግረዋል።   አስተዳደሩ ለግንባታው የሚውል ከሊዝ ነፃ 40 ሄክታር መሬት ማዘጋጀቱን ገልጸው፤ ግንባታው በአጠረ ጊዜ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ የሆኑ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉ ይደረጋል ብለዋል። መምህራን ሀገርን በመገንባትና ትውልድን በመቅረጽ በኩል እያበረከቱት ያለውን የማይተካ ሚና አድንቀው፤ ይህ የመኖሪያ መንደር ግንባታ ሲጠናቀቅ የመምህራንን የኑሮ ጫና ከመቀነስ ባለፈ፤ በትምህርት ጥራት ማስጠበቅ ላይ የሚኖራቸውን ተነሳሽነት ያሳድጋል ነው ያሉት።
የማኅበራዊ ሚዲያዎችን አጠቃቀም በአግባቡ ማድረግ እንደሚገባ ምሁራን አስገነዘቡ
Feb 4, 2026 46
ሐዋሳ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፡- ማኅበራዊ ሚዲያዎችን ለሀገር ዕድገትና ለገጽታ ግንባታ ማዋል በአግባቡ መምራት እንደሚገባ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ሥነ-ተግባቦት ምሁራን አስገነዘቡ። ማኅበራዊ ሚዲያን በአግባቡ መምራት ለሰላም፣ ለሀገር ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን በዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነትና ሥነ-ተግባቦት መምህር መሳይ ቦጋለ ለኢዜአ ገልጸዋል። በሌላ በኩል የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትና እንደሀገር የተያዙ ዕቅዶችን ማሳካት የሚያስችል ዕድል እንዳለው አመላክተዋል።   ሌላው የትምህርት ክፍሉ መምህር እያዩ ዓለማየሁ በበኩላቸው፤ በማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚተላለፉ መረጃዎች ያልተገባ መልክ እንዳይኖራቸው መንግሥት የዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀም ግንዛቤን ለዜጎች ማድረስ ላይ በይበልጥ እንዲሠራ መክረዋል። መንግሥት የጀመራቸው የኢትዮ-ኮደርስና የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂዎች ዘመኑን የዋጁ አሠራሮችን ለመዘርጋትና ለመተግበር ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥሩም አመላክተዋል። የዲጂታል ዓለሙን ዕድሎች በመጠቀም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማዕከል ያደረጉ ተግባራት ላይ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ይበልጥ እንዲሠሩ ማበረታታት እንደሚገባም ነው ምሁራኑ ያስገነዘቡት።
ኢኮኖሚ
የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን ደርሷል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Feb 4, 2026 26
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተገኝተው በመንግሥት የ6 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የዲጂታል ዘርፉ በተለይም የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አንስተዋል። ለውጡ ሲመጣ የሞባይል ተጠቃሚዎች ቁጥር 37 ሚሊዮን እንደነበር በመጥቀስ፥ አሁን ላይ በኢትዮ ቴሌኮም 87 ሚሊዮን በሳፋሪ ኮም ከ10 ሚሊዮን በላይ በድምሩ 97 ሚሊዮን የሞባይል ተጠቃሚዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ከለውጡ ወዲህ በ60 ሚሊዮን መጨመሩን ያሳያል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ሆኖም ይህ በቂ እንዳልሆነና እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሞባይል ተጠቃሚ እንዲሆን መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል። የ4 ጂ እና 5 ጂ ኔትወርክ አገልግሎት ተደራሽነት እየተስፋፋ መሆኑን አንስተው፥ 1 ሺህ 70 ከተሞች የ4 ጂ እንዲሁም 28 ከተሞች የ5 ጂ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህም ዜጎች የተሳለጠ ንግድና አገልግሎት እንዲያገኙ እያስቻለ ነው ብለዋል። በፋይናንስ ዘርፉ ከሦስት ዓመታት ወዲህ በሞባይል የገንዘብ ዝውውር የሚፈጽሙ ዜጎች ቁጥር 58 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ግብይት ስርዓቱም በጥሬ ገንዘብ ከሚደረግ ግብይት መብለጡን ጠቅሰው፥ ይህ የኢትዮጵያ የዝላይ ጉዞ የፖሊሲ ውጤት ስለመሆኑ አንስተዋል። በዲጂታል ክፍያ አገልግሎትም ባለፉት ስድስት ወራት የተመዘገበው ውጤት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነጻጸር በ60 በመቶ መጨመሩን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ገንዘብ ቁጠባና ብድር አገልግሎትም ማደጉን ነው ያስረዱት።  
በኮምቦልቻ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Feb 4, 2026 31
ኮምቦልቻ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ኮምቦልቻ ከተማ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። በኮምቦልቻ ከተማ ከሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነቡ ካሉ የልማት ፕሮጀክቶች ሶስቱ ተጠናቀው ለምረቃ በቅተዋል። የኮምቦልቻ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወንድወሰን ልሳነወርቅ በወቅቱ እንደገለጹት፣ በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን ከማምጣት ጎን ለጎን ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተፋጠነ ነው። በበጀት ዓመቱ በአቅመ ደካማ ዜጎች ቤት ግንባታ፣ በተማሪዎች ምገባ፣ የመስሪያና መሸጫ ሼዶች ግንባታን ጨምሮ ገበያን በማረጋጋት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ክትትልና ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል ። በከተማ አስተዳደሩ የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሲሳይ አየለ በበኩላቸው፣ በከተማዋ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የመንገድ፣ የትምህርት ቤት፣ የጤና ተቋማት እንዲሁም የውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል። ከሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነቡ ካሉ የልማት ፕሮጀክቶች ውስጥ የሰባት ነጥብ አምስት ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ፣ 45 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥና ሁለት ኪሎ ሜትር የኮብል ስቶን መንገድ ይገኝበታል ብለዋል። ዛሬ ግንባታቸው ተጠናቆ ለምረቃ የበቁት የወጣቶች መዝናኛ ሥፍራዎች፣ የመስሪያና የመሸጫ ሼዶች እንዲሁም የትምህርት ቤት መጸዳጃ ቤቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። አስተያየት ከሰጡት መካከል መሀመድ ሲራጅ እና አምሳለ ሀብታሙ የልማት ፕሮጀክቶቹ ለከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ አላቸው ብለዋል። በከተማዋ የሕብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በወቅቱ ተጠናቀው ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
የሸበሌ ሪዞርት ለክልሉ ተጨማሪ የቱሪዝም መዳረሻ በመሆን ለዘርፉ መነቃቃት ጉልህ ሚና ይጫወታል
Feb 4, 2026 106
ጅግጅጋ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦የሸበሌ ሪዞርት ለሶማሌ ክልል ተጨማሪ የቱሪዝም መዳረሻ በመሆን ለዘርፉ መነቃቃት ጉልህ ሚና እንደሚጫወት የክልሉ ነዋሪዎች ገለጹ። ኢትዮጵያ ባህላዊ፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ እምቅ የቱሪዝም ሀብት ባለቤት ብትሆንም ሀብቱን አውቆ፣ ለይቶና አልምቶ የገቢ ምንጭ ከማድረግ አኳያ ውስንነቶች እንደነበሩ ይታወሳል። የመደመር መንግስት ቱሪዝም ለሀገር ምጣኔ-ሀብት ዕድገትና ለገጽታ ግንባታ ያለውን ፋይዳ በመረዳት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እያከናወናቸው ባሉ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት መመዝገብ ጀምሯል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመሩት የገበታ ፕሮጀክቶችም አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ከማልማት ባለፈ ነባሮቹ እንዲታደሱና ለአካባቢው ተጨማሪ የገቢ አቅም እንዲሆኑ እያደረገ ነው። ከገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች መካከል ሰሞኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣በጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማርጌሌ እንዲሁም በሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐመድ በይፋ የተመረቀው የሸበሌ ሪዞርት አንዱ ነው። በ385 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በአንድ ጊዜ 400 እንግዶችን ማስተናገድ የሚችሉ ሦስት ምግብ ቤቶች፣ ልዩ የባሕል ማዕከል፣ ዘመናዊ የክብረ-በዓላትና የስብሰባ አዳራሾች፣ የሕፃናት መጫወቻ ስፍራዎችና 15 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸው የእግረኛ መንገዶችን ይዟል።   ኢዜአ ያነጋገራቸው የጅግጅጋ ነዋሪዎች ሪዞርቱ ለክልሉ ተጨማሪ የቱሪዝም መዳረሻ በመሆን ለዘርፉ መነቃቃት ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። ሪዞርቱ የሶማሌ ማህበረሰብን ባህላዊ አኗኗር በሚገልጽ መልኩ መገንባቱ ለአካባቢው ልዩ ገጽታን ከማላበስ ባለፈ የክልሉን የአኗኗር ዘይቤ በቀላሉ ለማስተዋወቅ የሚያስችል ነው ብለዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡ የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አብዱረህማን ኑህ ፤የሸበሌ ሪዞርት ለአካባቢው ተጨማሪ የቱሪዝም መዳረሻ በመሆን ለዘርፉ መነቃቃት ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብለዋል። መንግስት ለቱሪዝም መዳረሻ ልማት በሰጠው ትኩረት በየአካባቢው ያሉ ጸጋዎች እንዲወጡና ለዜጎች የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። ሸበሌን የመሳሰሉ ዘመናዊ ሪዞርቶች ግንባታ የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም ወሳኝ መሆናቸውን በማንሳት።   ሪዞርቱ የክልሉን ባህልና አኗኗርን ከማስተዋወቅ ባለፈ ለቱሪዝም ዘርፉ መነቃቃት ከፍተኛ ሚና እንዳለው የተናገሩት ደግሞ በሺር መሀመድ ናቸው። የአካባቢዉ ነዋሪዎቸ በክልሉ የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶችንና የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎችን በመጠበቅና በመንከባከብ ሃላፊነቱን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። የሸበሌ ሪዞርት 51 የመኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የቱሪስት አገልግሎት ይሰጣል።
የቦረና ላሞችን ከተሻሻሉ ዝርያዎች ጋር በማዳቀል የተሻለ የወተት ምርት የሚያስገኝ ውጤት ተገኝቷል
Feb 4, 2026 52
አዳማ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፡- የኦሮሚያ ግብርና ምርምር እንስቲትዩት የቦረና ላሞችን ከተሻሻሉ ዝርያዎች ጋር በማዳቀል የተሻለ የወተት ምርት እንዲሰጡ ለማድረግ የሚያስችል ውጤት ማግኘቱን ገለፀ።   በአዳሚ ቱሉ ግብርና ምርምር ማዕከል የቦረና ላሞችን የውጭ ዝርያ ካላቸው ኮርማዎች ጋር በማዳቀል የተሻለ የወተት ምርት የሚሰጡ ጊደሮች እንዲወለዱ ማድረግ መቻሉን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ተሾመ ቦጋለ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። ከቦረና ላሞች ጋር ተዳቅለው የተወለዱ ጥጆች አስተዳደጋቸው ፈጣን ከመሆኑ ባለፈ የተሻለ የወተት ምርት የሚሰጡ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ጥጆቹ በየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢ እንደሚላመዱና በአንድ ዓመት ተኩል ውስጥም መልሶ መውለድ እንደሚችሉ ተናግረዋል። የቦረና ላሞች በቀን የሚሰጡት የወተት ምርት ከ2 ሊትር እንደማይበልጥ አውስተው፤ በምርምር ማዕከሉ በማዳቀል የተወለዱ ጊደሮች ግን በቀን አስከ 10 ሊተር የወተት ምርት እንደሚሰጡ አስገንዝበዋል።   ዝርያቸው የተሻሻሉ 120 የመጀመሪያ ትውልድ የቦረና ጊደሮችን በስድስት ወራት ውስጥ ለተጠቃሚዎች እንዲደርሱ መደረጉንም አስታውቀዋል። በሁለተኛው ትውልድ በምርምር የተሻሻሉ ዝርያዎች ደግሞ በቀን ከ15 እስከ 20 ሊትር የወተት ምርት እንደሚሰጡ አመላክተዋል። በዚህም የወተት ምርትና ምርታማነትን ከመጨመር ባለፈ የአርሶ አደሩንና የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደተቻለ አስረድተዋል። በምሥራቅ ሸዋ ዞን አዳሚ ቱሉ ወረዳ የደስታ አቢጃታ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አማን ገመዳ፤ በምርምር ማዕከሉ ዝርያቸው ከተሻሻሉትና ከተዳቀሉት የቦረና ጊደሮች የተሻለ ምርት በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ዋሪዬ ደስታ እንደገለጹት፤ የተሻለ የወተት ምርት የሚሰጡ ጊደሮች በማግኘታቸው ያሏቸውን ከብቶች የተሻለ ምርት ወደ ሚሰጡት ዝርያዎች በመቀየር ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወጣቶች ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ እንዲያውሉ እያገዘ ነው 
Feb 4, 2026 89
ቦንጋ ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማወቅ በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል አስችሎናል ሲሉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቦንጋ ከተማ ወጣቶች አስታወቁ። የካፋ ዞን ኢንዱስትሪ እና ኢኖቬሽን መምሪያ በበጀት ዓመቱ ከ17 ሺህ በላይ ዜጎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመስጠት ማቀዱንም ገልጿል። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከወሰዱ የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወጣት መሠረት ገብረማርያም፤ መንግስት ያመቻቸውን ዕድል በመጠቀም በሁሉም ፕሮግራሞች ስልጠና በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆኑን ይናገራል።   ስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ከዚህ ቀደም ከነበረው የተሻለ እውቀት ለመጨበጥና አቅሙን በማሳደግ በተሰማራበት መስክ የላቁ ተግባራትን ለማከናወን እንዳስቻለው ነው የገለፀው። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እንደሀገር ትልቅ እድል ይዞ የመጣ እና በተለይ ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር አብረን እንድንራመድ ያደረገ ነው ያለው ደግሞ ሰልጣኝ ወጣት ድጋፌ ደምሴ ነው፣። በአራቱም ዘርፎች ስልጠናውን በመውሰድና የምስክር ወረቀት በመያዝ የሀገር ውስጥና የውጭ የኦንላይን የስራ እድሎችን አግኝቶ ተጠቃሚ መሆኑንም ነው የሚናገረው።   ስልጠናውን ዲጂታል ኢትዮጵያን ተግባራዊ ለማድረግ ለተያዘው እቅድ ስኬት የሰለጠነ፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን የመጠቀም አቅሙ የጎለበተ ዜጋን ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑንም ነው ያመለከተው። የካፋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ተፈሪ ታደሰ በበኩላቸው፤ በዞኑ በ2018 በጀት ዓመት ለ17 ሺህ 200 ዜጎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመስጠት እየተሰራ ነው ብለዋል።   ለዚህም ከመንግስትና ከግል የትምህርት ተቋማት፣ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከሚገኙ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን /ICT/ መምህራን ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ስድስት ወራትም አምስት ሺህ ዜጎች ስልጠና ወስደው ሰርተፊኬት መያዛቸውን አመልክተው በቀሪ ጊዜያትም ዕቅዱን ለማሳካት ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።
ዩኒቨርስቲው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን እውን ማድረግ የሚያስችሉ አዳዲስ የትምህርት መስኮችን ከፍቶ ሊያሰለጥን ነው
Feb 4, 2026 57
ጎንደር ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦የጎንደር ዩኒቨርስቲ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማፍራትና ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን እውን ማድረግ የሚያስችሉ አዳዲስ የትምህርት መስኮችን ከፍቶ ሊያሰለጥን መሆኑን አስታወቀ። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አፀደወይን (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣የትምህርት መስኮቹ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን እውን ማድረግ የሚችል የሰው ሃይል ለማፍራት ጉልህ ሚና አላቸው ብለዋል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ የዜጎችን ኑሮ ከማቃለል ባለፈ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት የሚጫወተውን ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ኢትዮጵያ አሳካዋለሁ ብላ የያዘቻቸው እቅዶች እውን እንዲሆኑ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሃይል ማፍራት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልዕኮ መሆኑንም አብራርተዋል። በዚህ ረገድ ጎንደር ዩኒቨርስቲ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮሩ አራት አዳዲስ የትምህርት መስኮችን ከፍቶ በሁለተኛ ዲግሪ ለማሰልጠን ተዘጋጅቷል ብለዋል። በትምህርት መስኮቹ ላይ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት መካሄዱን አስታውሰው፣ የሥርዓተ ትምህርት ቀረጻና ግምገማ መካሄዱንም ገልጸዋል። ዩኒቨርስቲው በተያዘው የትምህርት ዘመን ሁለተኛ መንፈቀ-ዓመት በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ በኮምፒውተር ኔት-ዎርክና ሴኩሪቲ፤ በዲጂታል ማርኬቲንግና ዲጂታል አናሊሲስ እንዲሁም በዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፎች ተማሪዎችን ማሰልጠን እንደሚጀምር አመልክተዋል። የትምህርት መስኮቹ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል በማፍራት ኢትዮጵያ ለጀመረችው ዲጂታል ጉዞ ውጤታማነት የጎላ ሚና እንደሚኖራቸውም አብራርተዋል። የጎንደር ዩኒቨርስቲ በመደበኛና በማታ የትምህርት መርሃ-ግብሮች ከ30 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት መስኮች እያሰለጠነ ይገኛል።
የኢትዮጵያን የግብርና ትራንስፎርሜሽን የሚያፋጥኑ የዲጂታል ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Feb 3, 2026 138
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦ በግብርናው ዘርፍ የተጀመረውን የዲጂታላይዜሽን ስራ የበለጠ የሚያጠናክሩ ውጤታማ ትግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ በግብርናው ዘርፍ የተጀመረውን የዲጂታላይዜሽን ስራ ይበልጥ የሚያጠናክርና መረጃዎችን በአንድ ቋት የሚያገናኝ "Ethiopia OpenAgriNet" የተሰኘ አዲስ ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል። ፕሮጀክቱ እስካሁን በተለያዩ ተቋማትና በተበታተነ መልኩ የሚገኙ የግብርና መረጃዎችን በአንድ የዲጂታል መረብ ውስጥ በማቀናጀት ለተጠቃሚዎች ምቹና ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።   በኢንስቲትዩቱ የኦፕሬሽን ሲነየር ዳይሬክተር ዳዊት ፊሊጶስ እንደገለጹት፣ አዲሱ ዲጂታል ሥርዓት አርሶ አደሮችን፣ የኤክስቴንሽን አገልግሎቶችን፣ የገበያ እና የአየር ንብረት መረጃዎችን እንዲሁም የፋይናንስ አገልግሎቶችን በአንድ ላይ የሚያስተሳስር ነው። ይህም ወቅታዊ መረጃዎችን በተለያዩ ቋንቋዎች ማግኘት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ስርዓቱ በተለይ በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ አወጣጥ ሂደትን ከመደገፉ ባለፈ፣ የአቅርቦት ሰንሰለቱን በማጠናከር ሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት አንስተዋል። መረጃን መሰረት ያደረገ የግብርና ውሳኔ አሰጣጥን ለማጎልበትና ዘርፉን በቴክኖሎጂ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተናግረዋል።   በኢንስቲትዩቱ የቴክኖሎጂ እና ዲጂታል ኢኖቬሽን ዳይሬክተር ግሩም ከተማ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ስርዓቱ ደህንነቱ የተጠበቀና ከሀገሪቱ የዲጂታል ስትራቴጂ ጋር በተጣጣመ መልኩ የተዘጋጀ እንደሆነ ጠቁመዋል። የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የግብርና ምርትን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ገልጸዋል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ ግብ የያዘው ይህ ፕሮጀክት፣ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ጉዞ በማፋጠን ዘርፉ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ሆኖ እንዲቀጥል የሚያስችል ነው ብለዋል።   ዲጂታል ስርዓቱን በትብብር ካዘጋጁት መካከል በዱባይ የፕሮቴን ኢንተርናሽናል የቢዝነስ ባለሙያ አሺሽ ቻተርጂ በበኩላቸው ዛሬ ይፋ የሆነው ፕሮጀክት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲሆን ትክክለኛና ወቅታዊ የአየር ሁኔታ፣ የገበያ መረጃ እና የግብርና ምክረ-ሀሳቦችን በቴክኖሎጂ አማካኝነት በቀላሉ ማግኘት ያስችላል ብለዋል። ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ጉዞ እንደሚያፋጥንም ገልጸዋል።
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ተንቀሳቃሽ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Feb 3, 2026 88
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018 (ኢዜአ)፦የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ተንቀሳቃሽ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ እያካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በተያያዘ በሰጡት ማብራርያ÷ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት አሁን ላይ 33 ማዕከላት ማድረስ እንደተቻለ ገልጸዋል። በቀጣይም የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት ዜጎች የመንግስትን አገልግሎት በተሻለ ጥራት እንዲያገኙ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የተጀመረበት ጊዜ አጭር ቢሆንም በዘርፉ ላይ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለ አስገንዝበዋል። የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ተንቀሳቃሽ አገልግሎት መስጠት መጀመር የሚያስችሉ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። በባሶች በመንቀሳቀስ ጭምር በተለዩ ቦታዎች በመንቀሳቀስ የኦን ላይን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል። የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትም የዜጎችን የመንግስት አገልግሎት ጥራትና ደረጃ በማሻሻል እንግልትን እየቀነሰ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።
ስፖርት
በኦስትራቫ በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው 
Feb 4, 2026 48
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድር ትናንት ማምሻውን በቼክ ሪፐብሊክ ኦስትራቫ ተካሂዷል። በሴቶች 1 ሺህ 500 ሜትር አትሌት ብርቄ ኃየሎም 4 ደቂቃ ከ00 ሰከንድ ከ62 ማይክሮ ሰከንድ አሸንፋለች። በ2026 በርቀቱ የዓለም ፈጣን ሰዓት አስመዝግባለች። ሳሮን በርሄ 4 ደቂቃ ከ01 ሰከንድ ከ23 ማይክሮ ሰከንድ ሁለተኛ፣ ሀገረወይን ካላዩ 4 ደቂቃ ከ01 ሰከንድ ከ92 ማይክሮ ሰከንድ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ሁለቱም አትሌቶች በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓታቸውን አስመዝግበዋል። ፅጌ ተሾመ 8ኛ እና አክሱማዊት አምባዬ 12ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን አጠናቀዋል።   በ800 ሜትር ሴቶች አትሌት ንግስት ጌታቸው 1 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ ከ98 ማይክሮ ሰከንድ አሸንፋለች። በ3 ሺህ ሜትር ሴቶች ኤርሚያስ ግርማ አራተኛ፣ ሚልኬሳ ፍቃዱ ሰባተኛ እና ወገኔ አዲሱ ዘጠነኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ጨርሰዋል። ፖርቹጋላዊው ኢሳቅ ናደር ፣ ደቡብ አፍሪካዊው ሼፖ ሺቴ እና ቤልጂየማዊው ጆን ሄይማንስ ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
ማንችስተር ሲቲ ከኒውካስትል ዩናይትድ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታቸውን ዛሬ ያደርጋሉ
Feb 4, 2026 71
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ካራባኦ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ የሁለተኛ ዙር መርሐ-ግብር ማንችስተር ሲቲ እና ኒውካስትል ዩናይትድ ይጫወታሉ። ጨዋታው ምሽት አምስት ላይ በኢትሃድ ስታዲየም ይከናወናል። ሁለቱ ክለቦች ጥር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ 2 ለ 0 ማሸነፉ አይዘነጋም። ማንችስተር ሲቲ የካራባኦ ዋንጫን ስምንት ጊዜ በማንሳት ከሊቨርፑል (10) ቀጥሎ ስኬታማው ክለብ ነው። ኒውካስትል ዩናይትድ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ነው። ሁለቱ ቡድኖች ከዚህ ቀደም በካራባኦ ዋንጫ ሁለት ጊዜ ተገናኝተው በተመሳሳይ አንድ አንድ ጊዜ አሸንፈዋል። ማንችስተር ሲቲ ለፍጻሜ ለማለፍ ማሸነፍ ወይም አቻ መውጣት በቂው ነው። ኒውካስትል ዩናይትድ የዋንጫ ክብሩን ለማስጠበቅ ከባድ ፈተና ከፊቱ ተጋርጦበታል። ኒውካስትል ከሁለት እና ከዚህ በላይ የግብ ልዩነት ማንችስተር ሲቲን ማሸነፍ ይኖርበታል። ቶኒ ሀሪንግተን ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ በፍጻሜው አርሰናል ጋር ይገናኛል። አርሰናል ትናንት ከቼልሲ ጋር ባደረገው የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ 1 ለ 0 በማሸነፍ በአጠቃላይ ድምር ውጤት ተጋጣሚውን 4 ለ 2 በመርታት ለፍጻሜ አልፏል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ይጫወታል 
Feb 4, 2026 66
አዲስ አበባ፤ ጥር 27/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ዛሬ ይጀመራል። ከቀኑ 9 ሰዓት ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሲዳማ ቡና በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው 18 ጨዋታዎች በስድስቱ አሸንፎ በአራቱ ተሸንፎ ስምንት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 11 ግቦችን በጨዋታዎቹ ላይ ሲያሳርፍ 10 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ26 ነጥብ 7ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና 18 ጨዋታዎችን አከናውኑ ዘጠኝ ጊዜ ሲያሸንፍ በሁለቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ ሰባት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 24 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ሲዳማ ቡና በ34 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች አላሸነፈም። ሲዳማ ቡና ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ሲዳማ ቡና ካሸነፈ በሊጉ የመጀመሪያ ዙር መሪ ሆኖ ያጠናቅቃል። በሌላኛው መርሐ-ግብር አዳማ ከተማ ከሃዋሳ ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። አዳማ ከተማ በውድድር ዓመቱ 18 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስቱን ሲያሸንፍ በሁለቱ ሽንፈት አስተናግዷል። 10 ጊዜ አቻ ወጥቷል። 15 ግቦችን በ18ቱ ጨዋታዎች ላይ 15 ግቦችን ሲያስቆጥር 12 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ28 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በሊጉ ካከናወናቸው 18 ጨዋታዎች መካከል ዘጠኙን ያሸነፈው ሃዋሳ ከተማ በበኩሉ አራት ጊዜ ተሸንፏል። አምስት ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። 20 ግቦችን ሲያገባ 10 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ሃዋሳ ከተማ በ32 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አቻ የወጣው አዳማ ከተማ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ሃዋሳ ከተማ ካሸነፈ ተከታታይ ድሉን ያስመዘግባል። ሀዲያ ሆሳዕና ከመቻል ከቀኑ 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።   አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ሀዲያ ሆሳዕና በ20 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። መቻል በ29 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ባለፉት ሁለት ተከታታይ የሊጉ ጨዋታዎች የተሸነፈው ሀዲያ ሆሳዕና ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። በ18ኛ ሳምንት በሸገር ከተማ 1 ለ 0 የተሸነፈው መቻል ማሸነፍ ወደ ድል መንገድ ይመልሰዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ የሚደረገው ጨዋታ ሸገር ከተማ እና ምድረ ገነት ሽሬን ያገናኛል። ሸገር ከተማ በ20 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ምድረ ገነት ሽሬ በ22 ነጥብ 11ኛ ላይ ተቀምጧል። በ18ኛ ሳምንት መቻል ያሸነፈው ሸገር ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አቻ የወጣው ምድረ ገነት ሽሬ ማሸነፍ የመጀመሪያውን በደረጃ ሰንጠረዥ ከወገብ በላይ ይዞ እንዲያጠናቅቅ ሊያደርገው ይችላል። የ19ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር እስከ ጥር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የቅዱስ ጊዮርጊሱ አቤል ያለው እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ አዲስ ግደይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በጋራ እየመሩ ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የሐረማያ ሐይቅ የቱሪስት መዳረሻነት የማበልጸግ ስራ በተቀናጀ መንገድ በመከናወን ላይ ይገኛል
Feb 2, 2026 102
ሐረማያ ፤ጥር 25/2018 (ኢዜአ) ፡-የሐረማያ ሐይቅን የቱሪስት መዳረሻነቱን የማበልጸግ ስራ በተቀናጀ መልኩ እየተካሔደ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ። በማያ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙት የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል የሐረማያ ሃይቅ እንዱ ነው። ለበርካታ ዓመታት ደርቆ የነበረው ሐይቁ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች ትኩረት ተደርጎ በመከናወናቸው ወደ ቀድሞው ይዞታው መመለስ ችሏል። የከተማ አስተዳደሩ እና የአካባቢው ማህበረሰብ ሃይቁን እያለማውና እየተንከባከበው በመሆኑም የጎብኚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ጀሚላ ሲምቢሩ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ሐይቁ ከመዝናኛነቱ ባለፈ ለወጣቶች የስራ እድል እየፈጠረ የሚገኝ ሲሆን በዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የማጎልበት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። አካባቢው ትልልቅ እሴቶችና ጸጋዎች የሚገኙበትና በኪነ ጥበቡም ዘርፍ ስመ-ጥር አርቲስቶች የፈለቁበት መሆኑንም ይገልፃሉ። የአካባቢውን ባህል፣ ኪነ ጥበቡብና ቱሪዝሙ ዘርፉን እንደ አንድ ጸጋ በመጠቀምና ከቱሪዝም ጋር በማሰናሰል የዘርፉን ኢኮኖሚ ማሳደግና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።   የማያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢፍራህ ወዚር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በአፈርና ውሃ ጥበቃ እና በአረጓዴ አሻራ ስራ የተመለሰውን የሐረማያ ሃይቅ አጠቃቀምን የማስተካከል፣ የመጠበቅና የመንከባከብ ስራ እየተከናወነ ይገኛል። ሐይቁ ወደ ቀድሞ ቦታው መመለሱ ለጎብኚዎች እርካታን ከማጎናጸፉ ባለፈ ለአካባቢው ነዋሪዎችና ለወጣቶች የገቢ ምንጭ እየሆነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የሐረማያ ሐይቅ በተደረገለት እንክብካቤ ውብና ማራኪ የቱሪስት ቀልብ የሚስብ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፤ ለወጣቶችም የገቢ ምንጭ ማግኛ ሆኗል ያለው ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የቱሪዝም ባለሙያ ኦሊያድ በሪሶ ናቸው።   በአካባቢው ባለሀብቶችን በመጋበዝ ሎጆችና ሪዞርቶች በማስፋፋት የተሻሉ ስራዎችን መስራት እንደሚቻልም ነው አቶ ኦሊያድ አስተያየታቸውን የሰጡት።   በሐረማያ ሐይቅ ላይ የጀልባ አገልግሎት የሚሰጠው ወጣት ሙርቲ አህመድ፤ጎብኚዎችን በጀልባ ከማስጎብኘት ስራ በተጨማሪ በአሳ ልማት ስራም መሰማራቱን ይገልፃል።    
በአማራ ክልል የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ምርታማነት እንዲጎለብት አግዘዋል
Feb 2, 2026 148
‎ባህር ዳር፤ጥር 25/2018 (ኢዜአ)፡- አማራ ክልል የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነት እንዲጎለብት እገዛ ማድረጋቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ‎የቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት፤ ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራዎች የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነት እንዲያድግ አግዘዋል። ‎ስራውን በማስቀጠልም ‎በያዝነው የበጋ ወራት በተለዩ ዘጠኝ ሺህ 206 ተፋሰሶች በ456 ሺህ 411 ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ለማከናወን ግብ ተይዞ ወደ ተግባር ተገብቷል።   ‎እስካሁን በተደረገ ጥረትም የዕቅዱን 37 በመቶ ማከናወን እንደተቻለ ጠቅሰው፤ በዚህም ከ3 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልፀዋል። ‎ከዚሁ በተጓዳኝም ለመጪው ክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ የሚሆን ቦታ የመለየትና ለተከላ የሚውል ከ አንድ ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን አንስተዋል። በተቀናጀ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ ላይ ከተሰማሩ አርሶ አደሮች መካከል ‎በደቡብ ጎንደር ዞን የፋርጣ ወረዳ አርሶ አደር ዓለሙ መንጌ በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ከህልውና ጋር የተያያዘ መሆኑን በመረዳት ተግባሩን በማጠናከር በየዓመቱ በራሳቸው ተነሳሽነት እያከናወኑ መሆናችውን አንስተዋል። ‎ዘንድሮም በቀበሌያቸው በተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ላይ በንቃት በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በቀበሌያቸው ያከናወኑት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የመሬቱን ለምነት በመመለስ ለምርታማነት ማደግ አስተዋጽኦ እንዳበረከተላቸው የገለፁት ደግሞ ‎ሌላኛው የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ካሳሁን መንግስት ናቸው። ቀደም ሲል የተሰራው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ግማሽ ሄክታር የእርሻ ማሳቸውን ለምነት በመመለሱ እስከ አምስት ኩንታል ተጨማሪ ምርት እንዲያገኙ ማስቻሉን ገልፀዋል። የልማት ስራው ተጠቃሚነታቸውን በተጨባጭ እያሳደገ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ላይ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። ‎በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተከናወነ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራም የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባሻገር በግብርና ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ እንዳስቻለም ተመላክቷል።  
የአረንጓዴ አሻራ፣ የተፋሰስ ልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች የውሃ አዘል መሬቶችን ከመጠበቅ አኳያ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ ነው
Feb 2, 2026 127
አዲስ አበባ፤ ጥር 25/2018 (ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ፣ የተፋሰስ ልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች የውሃ አዘል መሬቶችን ከመጠበቅ አኳያ ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ገለጸ፡፡ ባለስልጣኑ የዘንድሮውን የዓለም የውሃ አዘል መሬቶች ቀን "የውሃ አዘል መሬት እና ሀገር በቀል እውቀት፤ የባህል ቅርሳችንን እናክብር" በሚል መሪ ቃል እያከበረ ይገኛል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የተለያዩ የውሃ አዘል መሬቶች እና የብዝሃ ህይወት ባለቤት ናት።   እነዚህ ተፈጥሯዊ ጸጋዎች ተጠብቀው ለትውልድ እንዲሸጋገሩም ሀገር በቀል እውቀት እና ባህላዊ የጥበቃ ስልቶች ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የውሃ አዘል መሬቶች ከፍተኛ ጥቅም እያስገኙ መሆኑን ጠቁመው የተበከለ ውሃን በተፈጥሯዊ መንገድ ማጣራት፣ የጎርፍ አደጋን መከላከል እና የአፈር እርጥበትን መጠበቅ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም እና የአካባቢን ሙቀት መቀነስን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በእነዚህ ወሳኝ የተፈጥሮ ሃብቶች ላይ የሚደርሱ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ዘመናዊውን ሳይንሳዊ እውቀት ከሀገር በቀል ጥበብ ጋር አቀናጅቶ መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተተገበሩ ያሉ የአረንጓዴ አሻራ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች ለውሃ አዘል መሬቶች ደህንነት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን አረጋግጠዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ደን ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቴ ግጄ፤ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ ውሃ አዘል መሬቶችን የመለየትና ተገቢውን ጥበቃ የማድረግ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   የአማራ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ደን ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ በልስቲ ፈጠነ በበኩላቸው፤ በክልሉ የሚገኙ የውሃ አዘል ስፍራዎችን በዘላቂነት ለማልማት ዘመናዊ ሳይንሳዊ ዕውቀቶችን ከባህላዊ ጥበቃ ዘዴዎች ጋር በማቀናጀት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።   ማህበረሰቡ ስለ እርጥብ መሬቶች ፋይዳ ያለውን ግንዛቤ እንዲያሳድግና ከሀብቱ በሥርዓት ተጠቃሚ እንዲሆን ሰፊ የትምህርትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኦሮሚያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኢዳቲ ጠቁመዋል።
በዞኑ አርብቶ አደሩን በማሳተፍ ከ33 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው
Jan 31, 2026 148
ጂንካ፤ ጥር 23/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሩን በማሳተፍ ከ33 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የአፈርና ውሃ ጥበቃና የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ ምንላርገው አዲሱ፣ በዞኑ በተጀመረው የተፋሰስ ንቅናቄ ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት 50 ንዑስ ተፋሰሶች የማልማት ስራ እንዲሁም በአርብቶ አደርና በዝቅተኛ አካባቢዎች ደግሞ ከ17 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።   በአጠቃላይ በዞኑ ከ33 ሺህ ሄክታር መሬት የተፋሰስና የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፥ የተፋሰስ ልማቱ በተከናወነባቸው ስፍራዎች ከ11 ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተከላ ይከናወናል ነው ያሉት። በዘንድሮው ዓመት የተፋሰስ ልማት በሳይንሳዊ ጥናት የተደገፈ ስነ-አካላዊና ስነ-ህይወታዊ ስራዎች እንደሚከናወኑም ጠቁመዋል። ልማቱ የተከናወነባቸው አካባቢዎችን ከሰውና ከእንሰሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በዞኑ ሐመር ወረዳ እየተከናወነ ባለው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተሳተፉት ወይዘሮ አልጎ በሌ፥ በአካባቢው የቡስካ ጥብቅ ደን እንደሚገኝ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ደኑ በሰውና በእንስሳት ጉዳት ይደርስበት እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ደኑን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ የመጠበቅ ስራ ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። በአካባቢያችን የተፋሰስ ልማት ከተጀመረ ወዲህ አካባቢው ለእርሻ ተስማሚ መሆን ጀምሯል ያሉት አቶ አስ ኦቶሎ ለእንስሳት የሚሆን በቂ የግጦሽ ሳር የምናገኝበት ዕድልንም እየፈጠረ ነው ብለዋል።      
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ የምታስተናግዳቸው አህጉራዊ ሁነቶች
Feb 4, 2026 168
በሙሴ መለሰ የዓለም ስርዓት በፍጥነት እየተቀያየረ ይገኛል። አፍሪካ በዚህ ተለዋዋጭ ስርዓት ውስጥ የሚገባትን ቦታ የመያዝ ጉዳይ የመነጋገሪያ አጀንዳ ከሆነ ሰነባብቷል። አፍሪካ በርካታ ወጣት የያዘች እና ብዝሃ የተፈጥሮ ፀጋዎች ያሏት አህጉር ናት። በአፍሪካ ተግባራዊ የተደረገው አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በቀጣናው የንግድ ትስስርን በማሳለጥ እድገትን የማፋጠን ተስፋ ተጥሎበታል። አፍሪካ እድሎቿን በሚገባ ለመጠቀምና የሚስተዋሉ ፈተናዎቿን ለመሻገር ምላሽ የምትሰጥበት የልማት እና እድገት ጉዞዋን ከመበየን ባለፈ በዓለም መድረክ የሚኖራትን ሚናም ይወስናል። በአህጉር ደረጃ የተቀመጡ እንደ አጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ያሉ አህጉራዊ ማዕቀፎች እንዲሳኩ ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። መንግስታት፣ የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮች ትብብራቸው ማጠናከር ይኖርባቸዋል።   የተገቡ ቃልኪዳኖችን ወደ ሚለካ ውጤት ለመቀየር ዘላቂነት ያለው አመራር ሰጪነት፣ ኢንቨስትመንትን ማጠናከር እና ተከታታይነት ያለው ውይይቶችን ማድረግ ይገባል። ውሳኔ ሰጪዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኙ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ መድረኮች በአጀንዳዎች ላይ የተቀናጀ የተግበባር ምላሽ ለመስጠት ቁልፍ ሚና አላቸው። አፍሪካ እድሎቿን በመጠቀም እና ፈተናዎቿን በማለፍ መንገድ ላይ በሆነችበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ ሁለት ወሳኝ አህጉራዊ ሁነቶችን ታስተናግዳለች። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የመሪዎች ጉባኤ መሪ ሀሳብ ነው።   ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። የመሪዎች ጉባኤው በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ያስተላልፋል ተብሎም ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ኮሚቴ ተወካዮች (PRC) ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ መክሯል።   ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን አቅርቧል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። ከአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ማግስት ሌላኛው በኢትዮጵያ የሚካሄደው ዘጠነኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ነው። የቢዝነስ ፎረሙ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(ኢሴኤ) ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሁነቱን አዘጋጅተውታል። “የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ በፋይናንስ መደገፍ፤ ስራ እና ኢኖቬሽን ለዘላቂ ትራንስፎርሜሽን” የፎረሙ መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም በአፍሪካ የልማት እና የኢኮኖሚ እድገት ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን በማድረግ በየዓመቱ የሚካሄድ ከፍተኛ አህጉራዊ የምክክር መድረክ መሆኑን የኢሲኤ መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ አጋርነትና የኢንቨስትመንት መጠንን ማሳደግ በተለይም የመንግስት እና የግል የተቀናጀ የፋይናንስ አቅርቦትን ጨምሮ የተለያዩ የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይወያያል። የወጣቶችን የኢኖቬሽን ስራ ከፋይናንስ አቅርቦት ጋር የሚያስተሳስር የአፍሪካ የወጣቶች አይበገሬነትና ትራንስፎርሜሽን ማዕቀፍ ይፋ ይሆናል። በኢሲኤ የበለጸገውና የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ ቃል ኪዳኖችን ትግበራ የሚከታታልና የሚቆጣጠር ስርዓትም በፎረሙ ይፋ ሆኖ ወደ ትግበራ ይገባል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው ሁነት ላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የምክክር መድረኮችና የባለሙያዎች ውይይቶች ይደረጋሉ።   አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጣራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ አውደ ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። ከአህጉራዊ ሁነቶቹ ባሻገር የባለብዙ ወገን መድረክ የሆነው የአፍሪካ እና ጣልያን ጉባኤ የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ሁነቶቹን ማዘጋጀቷ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ጸንቶ የቆየውን የመሪነት ሚናዋን እንዲሁም የአህጉራዊ ምክክር፣ የባለብዙ ወገን ውይይቶችና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባት ማዕከልነቷንም አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ በኮሪደር ልማት እና በከተማ ማዘመን ስራ በፍጥነት እየተለወጠች ሲሆን የሁነቱ ተሳታፊዎች ከስብሰባው ባለፈ የመዲናዋን አዲስ መልክ የመመልከት እድል ያገኛሉ። የእነዚህ አህጉራዊ ስብሰባዎች ስኬት የሚለካው በአቋም መግለጫ ሳይሆን አጋርነትን በማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና የሚጨበጥ ውጤት በአህጉሪቱ በማስመዝገብ ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ የምታዘጋጃቸው አህጉራዊ ሁነቶች አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጣራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ አውደ ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። ከአህጉራዊ ሁነቶቹ ባሻገር የባለብዙ ወገን መድረክ የሆነው የአፍሪካ እና ጣልያን ጉባኤ የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ሁነቶቹን ማዘጋጀቷ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ጸንቶ የቆየውን የመሪነት ሚናዋን እንዲሁም የአህጉራዊ ምክክር፣ የባለብዙ ወገን ውይይቶችና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩባት ማዕከልነቷንም አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ በኮሪደር ልማት እና በከተማ ማዘመን ስራ በፍጥነት እየተለወጠች ሲሆን የሁነቱ ተሳታፊዎች ከስብሰባው ባለፈ የመዲናዋን አዲስ መልክ የመመልከት እድል ያገኛሉ። የእነዚህ አህጉራዊ ስብሰባዎች ስኬት የሚለካው በአቋም መግለጫ ሳይሆን አጋርነትን በማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን በማሳደግና የሚጨበጥ ውጤት በአህጉሪቱ በማስመዝገብ ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ የምታዘጋጃቸው አህጉራዊ ሁነቶች አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች።
በኒጀር በደረሰ ጥቃት መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው የአስካይ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ተጠግነው በቅርቡ አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ
Feb 3, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ጥር 26/2018(ኢዜአ)፦ በኒጀር ዋና ከተማ በደረሰ ጥቃት መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት የአስካይ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ተጠግነው በቅርቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ ፡፡ አየር መንገዱ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው ማብራሪያ ባለፈው ሐሙስ ጥር 21/ 2018 ዓ.ም ሌሊት በኒጀር ዋና ከተማ ኒያሚ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰው ጥቃት ሁለት የአስካይ አየር መንገድ ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ፡፡ አውሮፕላኖቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አጋር የሆነው የአስካይ አየር መንገድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት ከአውሮፕላን አከራዮች የተከራያቸው እና በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የተመዘገቡ መሆናቸውን አስረድቷል፡፡ በአውሮፕላኖቹ ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመገምገም የተላከው የቴክኒክ ቡድን ጉዳቱ መጠነኛ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን አውሮፕላኖቹ ተጠግነው በቅርቡ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡም ተገልጿል ::
የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም አጋርነታቸውን ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Feb 2, 2026 97
አዲስ አበባ፤ጥር 25/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም ሰላምና ልማትን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች አጋርነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር ጋር በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተወያይተዋል። ውይይቱ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ በቆየው የአፍሪካ እና ዩናይትድ ኪንግደም አጋርነት ያተኮረ ነው። ሁለቱ ወገኖች የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እና ህግን መሰረት ያደረገ ዓለም አቀፍ ስርዓት ለመጠበቅ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።   የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ዩናይትድ ኪንግደም ከአፍሪካ ጋር ያላትን የረጅም ጊዜ ትስስር ያደነቁ ሲሆን በዓለም ላይ ያላትን ገንቢ ሚና እና ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ጋር በጤና፣ ትምህርት፣ የአየር ንብረት ምላሽ እና ንግድ ያላትን ትብብር አንስተዋል። ሀገሪቷ ለአፍሪካ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) በአደጋ ጊዜ ዝግጁነት እና ምላሽ እንዲሁም በሶማሊያ ለአፍሪካ ህብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) ድጋፍ እያደረገች እንደምትገኝም አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር የአፍሪካ ህብረት በዓለም ዲፕሎማሲ፣ ቀጣናዊ ሰላም እና ልማት ያለውን ሚና አድንቀዋል። ሁለቱ ወገኖች የአፍሪካ ህብረት እና ዩናይትድ ኪንግደም በሱዳን፣ በሳሄል ቀጣና እና በሶማሊያ ያለውን የአፍሪካ ህብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሀገራት ለውኃ አቅርቦት፣ ጥራት እና ለንጽህና መሰረተ ልማቶች ቅድሚያ መስጠት ይጠበቅባቸዋል
Feb 1, 2026 211
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ሁሉም ሀገራት ለውኃ አቅርቦት፣ ለጥራት እና ለንጽህና መሰረተ ልማቶች ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው የአፍሪካ ሕብረት አስገነዘበ። በሕብረቱ የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ጥበቃ ኮሚሽነር ሙሴ ቪላካቲ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አህጉራዊው የግብርና ልማት ፕሮግራም ባለፉት 20 ዓመታት በአባል ሀገራት ዘንድ ጉልህ ለውጦች ማምጣቱን ገልጸዋል።   ይህም አባል ሀገራት ጠንካራ የግብርና ዕቅድ ሥርዓት እንዲዘረጉ፣ ውጤታማ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም ቀረፃ እንዲኖራቸው እና በምርትና ምርታማነት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማገዙን አንስተዋል። ፕሮግራሙ ትኩረት የሚያደርገው በተለይም በምርት መጠንና በምርታማነት ዕድገት ላይ በመሆኑ፤ በአሁኑ ወቅት በበርካታ ሀገራት ውስጥ የሚታየው የምርት መጠን መጨመር የዚሁ ጥረት ውጤት ነው ብለዋል። ማንኛውም የልማት እንቅስቃሴ ከውኃ ጋር የተቆራኘ መሆኑን አስገንዝበው፤ ግብርናን፣ ኢነርጂን ወይም ጤናን ስናስብ ሁሉም ነገር ከውኃ ጋር የተያያዘ ነው፤ ስለዚህ ውኃ ለዘላቂ ልማት እጅግ ወሳኝ ነው ብለዋል።   ለዚህም ነው “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የሚለው መሪ ሐሳብ ለ39ኛው የሕብረቱ መሪዎች ጉባዔ የተመረጠው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ጉዳዩ በሕብረቱ አጀንዳነት የተያዘው በአህጉሪቱ ያለውን የውኃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል። በአህጉሪቱ ወደ 400 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች መሰረታዊ የውኃ አገልግሎት እንደማያገኙ ጠቁመው፤ ከ700 ሚሊየን የሚልቁትም ደኅንነቱ የተጠበቀ የጽዳት አገልግሎት የላቸውም ብለዋል። ይህ የአገልግሎት እጥረት በሰዎች የዕድገትና የአህጉሪቱ የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ትልቅ እንቅፋት መሆኑንም አመላክተዋል። ውኃን እንደ ትምህርት፣ ጤና እና ግብርና ትልቅ ትኩረት ሰጥተን ብንሠራበት ኖሮ ይህንን ችግር በቀላሉ መፍታት እንችል ነበር ያሉት ኮሚሽነሩ፤ አሁን ላይ ጉዳዩ ትኩረት በማግኘቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።   በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ዋነኛ ግብ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መሆኑን ተናግረው፤ የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮግራም 45 በመቶ የሚሆነውን የግብርና ምርት በአፍሪካ ለማምረት ግብ ይዞ እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። በተጨማሪ የአፍሪካን የውኃ አካላት ሀብት ወይም ብሉ ኢኮኖሚን ሙሉ በሙሉ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሆነ አንስተው፤ ይህ ዘርፍ ለአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራና ለኢኮኖሚ መነቃቃት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል ነው ያሉት። የአፍሪካን የሰብል ዝርያዎች መጠበቅ መቻል የአህጉሪቱ ኅልውና ጉዳይ መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸው፤ ለዚህም ጠንካራ የዘር ባንኮች ሊኖሩን ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
ሐተታዎች
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 398
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ።   በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 742
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 692
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 903
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 749
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 713
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1313
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3625
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3286
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2129
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7937
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6424
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60036
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54017
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34631
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32193
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27486
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26433
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25961
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25778
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60036
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54017
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34631
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32193
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ዕድሜ  ያልገደበው የልማት አርበኝነት 
Jan 14, 2026 415
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት ብርቱዎች ነገን በማሰብ ሁሌም ታትረው ይሰራሉ፤ ይደክማሉ፤ ይጥራሉ…ለቀጣዩ ትውልድም ጥሪት በማስቀመጥ አሻራቸውን ያኖራሉ። አገር የምትገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው። “አባት ያበጀው፤ ለልጅ ይበጀው” እንደሚባለው ልጆች ከአባቶቻቸው ያገኙትን ጥሪት በአዲስ እውቀትና አሰራር ለአገር እድገት በሚበጅ መልኩ አጠናክረው መጠቀማቸው አይቀርም። “ዕድሜ ጸጋ ነው” የሚለው አባባል አንዳንዴ በዕድሜ ብንገፋም ጠንክረን ከሰራን ብዙ ነገር እናያለን ከሚለው ጋር የተያያዘ ነው። በሰቆጣ ከተማም እድሜ ሳይገድባቸው በልማት ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ለዚህ ማሳያ ናቸው። የከተማዋ ነዋሪ የ67 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ አወቀ እና የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ዕድሜያቸው ቢገፋም ጠንክሮ ከተሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና ዕድሜ ጸጋ ሆኖ ብዙ ለውጥ ማየት እንደሚቻል ማሳያ ናቸው። ግለሰቦቹ ከዕድሜ ብዛት ጉልበቴ ደከመ፣ አይኔ ፈዘዘ፣ እጄም ተሳሰረ…ሳይሉ ጊዜያቸውን በደን፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ በማሳለፍ ለወጣቶች የልማት አርአያነት ያለው ተግባር እየፈጸሙ ነው። አቶ ብርሃኑ አወቀ በሰቆጣ ከተማ ዳርቻ የሚገኝ አለቱ ያገጠጠና የተራቆተ አካባቢን ከሌላ አካባቢ ለም አፈር በማምጣትና በመደልደል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ደን በማልማት ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ነው።   ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከወጣሁ ጀምሮ ጠንክሬ በመስራት የምለወጥበትን ሥራ ማሰብ ስነበረብኝ፤ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ለዘመናት የቆየን ጭንጫ መሬት ጠርጌና ደልድዬ ማልማት ችያለሁ ይላሉ ወደኋላ መልስ ብለው የተነሱበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ። ግማሽ ሄክታር በማይሞላ መሬት ላይ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ዘይቱና፣ ጌሾ፣ ቡና፣ ማንጎና አቮካዶ አልምተዋል። በተጨማሪም ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና ሽንኩርት በማምረት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ጥሪት አፍርተዋል።   ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ተግቶ መስራት ከተቻለ ሀብት ማፍራትና ህይወትንም መለወጥ እንደሚቻል የገለጹት አቶ ብርሀኑ፣ ወጣቱም ከእሳቸው የሥራ ትጋት በመማር በአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ሊጠቀም ይገባል ሲሉ ይመክራሉ። ሌላው የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ባለፉት 18 ዓመታት በተሰማሩበት የአትክልትና ደን ልማት ሥራ የአካባቢያቸውን ገጽታ ቀይረዋል። የዕድሜ ዘመናቸውን በውትድርናና በመንግስት ሠራተኝነት በማገልገል ሃገራዊ ግዳጃቸውን ሲወጡ ነው የቆዩት።   ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከተገለሉ በኋላም ቤት ውስጥ መቀመጥን አልመረጡት። አካፋና ዶማቸውን ይዘው ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ ጌሾ፣ ዘይቱና እና ማንጎ በማልማት ምርቱን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። በአካባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ለይተን ማልማት ከቻልን ድህነትን ማስወገድ የሚከብድ አይሆንም ያሉት አቶ ታደሰ፣ የተራቆተና በጎርፍ የተጎዳን መሬት በማልማት አካባቢውን ሳቢና ማራኪ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት። ወጣቱም ከእሳቸው አርአያነት ያለው ተግባር በመማር በአካባቢው እጁ ላይ ባለ ሀብት ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ማሳየት እንዳለበት መክረዋል።   የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ እንደገለጹት፤ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 24ሺህ 847 አርሶ አደሮች በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል ዕድሜ ሳይገድባቸው ወደ ልማት የገቡ አረጋዊያን እያከናወኑት ያለው የግብርና ልማት ሥራ ለወጣቱ ትልቅ ትምህርት እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከእነሱ ልምድ በመውሰድ በዞኑ ወጣቶች፣ ሴቶችና አረጋዊያን በጓሮና ባላቸው መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህም በዞኑ የሚስተዋለውን የስርዓተ ምግብ ችግር ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
ከማላጋ እስከ አፍሪካ ዋንጫ፤ የሞሮኮው አዲስ እንቁ ብራሂም ዲያዝ
Jan 13, 2026 415
  የግል ክህሎት፣ ፈጣን አስተሳሰቡ እና በጠባብ ክፍተቶች ውስጥ ሰብሮ የመግባት አቅሙ ሙገሳ እንዲጎርፍለት አድርጓል። አንድ ለአንድ ሲገናኝ ተከላካዮችን በፈጣን አካላዊ ቅልጥፍና እና በድንገት አቅጣጫ በመቀየር የሚያልፍበት መንገድ እንዲሁም የመፍጠር አቅሙ የተመልካቾችን ቀልብ የሚይዝ ነው። የአማካይ እና የአጥቂ መስመርን በማገናኘት እና በአስገራሚ ሁኔታ አጭር ኳሶችን በማቀበልም የተዋጣለት ተጫዋች ነው ማለት ይቻላል። በቦታ አያያዙ የእግር ኳስ ልኅቀቱ ከፍተኛ ነው የሚል አድናቆት ከእግር ኳስ ባለሙያዎች አግኝቷል። ኳስን ሲያንከባልልም ለዐይን ይስባል። ከክህሎቱ እና ከማራኪ እንቅስቃሴው ባለፈ ወደ ኋላ እየመለሰ ተከላካዮችን ያግዛል፣ ኳስ ይነጥቃል። ይህ ተጫዋች የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ክስተት የሆነው የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ ነው። የ26 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አምስት ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ነው። አዘጋጇ ሞሮኮ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ኮሞሮስን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የውድድሩን የመጀመሪያ ግብ አስቆጥሯል።   ብራሂም አብዱልቃድር ዲያዝ የተወለደው እ.አ.አ ኦገስት 3 ቀን 1999 በስፔን ማላጋ ግዛት ነው። እናቱ ስፔናዊ አባቱ ሞሮኳዊ ናቸው። ዲያዝ ያደገው በማላጋ ነው። እግር ኳስንም በአንዳሉሺያዊቷ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል። በ16 ዓመቱ ካደገበት ማላጋ በመውጣት እ.አ.አ በ2015 ወደ ማንችስተር ሲቲ ወጣት አካዳሚ በ200 ሺህ ፓውንድ ወጪ ተዘዋወረ። ዲያዝ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2016 በካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ ሊግ ካፕ) ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ባደረገው ጨዋታ በ80ኛው ደቂቃ በኬሌቺ ኢናቺዩ ተቀይሮ በመግባት ለውኃ ሰማያዊዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያውን ጨዋታ ካደረገ ከሶስት ቀናት በኋላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለሶስት ዓመታት የሚያቆየውን ፕሮፌሽናል ኮንትራት ተፈራርሟል። እ.አ.አ ኖቬምበር 21 ቀን 2017 ማንችስተር ሲቲ ከፌይኖርድ ሮተርዳም ጋር ባደረገው የሻምፒዮናስ ሊግ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል። በወቅቱ ብራሂም ስተርሊን መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰዓት ላይ ነበር ተቀይሮ የገባው። ዲያዝ በውኃ ሰማያዊዎቹ ማልያ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የተጫወተው እ.አ.አ ዲሴምበር 19 ቀን 2017 ነው። ማንችስተር ሲቲ ከሌስተር ሲቲ በካራባኦ ካፕ ጨዋታ ላይ ለ88 ደቂቃዎች ተሰልፎ ተጫውቷል።   እ.አ.አ ጃንዋሪ 20 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በወቅቱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ያነሳ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ አራት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ተሳትፎ ያደረገው ብራሂም ዲይዝ የሜዳሊያ ሽልማት አግኝቷል። እ.አ.አ ኦገስት 5 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን 2 ለ 0 ባሸነፈበት የኮሙዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ላይ በፊል ፎደን ተቀይሮ በመግባት ለ15 ደቂቃዎች ተጫውቷል። ዲያዝ እ.አ.አ 2018/19 ማብቂያ ላይ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የመጀመሪያ ግቦቹን ለሲቲ አስቆጥሯል። በማንችስተር ሲቲ ያለው ውል እ.አ.አ 2019 ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት ይነሳ ነበር። ዲያዝ እ.አ.አ ጥር 2019 በ17 ሚሊዮን ዩሮ ከማንችስተር ሲቲ ወደ ሪያል ማድሪድ ተዘዋወረ። ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም ፈርሟል። የክንፍ ተጫዋቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን በነጮቹ ማልያ ያደረገው እ.አ.አ ጥር 9 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ ሌጋኔን በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ 3 ለ 0 ባሸነፈበት ወቅት ነው። ከአራት ቀናት በኋላ በስፔን ላሊጋ ሪያል ማድሪድ ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ ተቀይሮ በመግባት በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያ ግቡን ለማስቆጠር ሶስት ወራትን ጠብቋል። እ.አ.አ ግንቦት 12 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በሪያል ሶሲዬዳድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በወቅቱ ዲያዝ ስድስት ጨዋታዎች ላይ በላሊጋው የተጫወተ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዓመቱ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እ.አ.አ በ2021/21 የውድድር ዓመት ብራሂም ዲያዝ ወደ ኤሲ ሚላን በውሰት ማምራቱን ይፋ አደረገ። ዲያዝ ሚላን እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2020 ክሮቶኔን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ የመጀመሪያ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ ግንቦት 2021 ኤሲ ሚላን ጁቬንቱስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ያስቆጠረው ግብም ተጠቃሽ ነው። ዲያዝ በኤሲ ሚላን የውሰት ውሉ ሲያበቃ በድጋሚ ለሁለት ዓመታት በውሰት የሚቆይበት ስምምነት ሪያል ማድሪድ ከጣልያኑ ክለብ ጋር የተፈራረመ ሲሆን፤ ውሉ ሚላን ተጫዋቹን የማቆየት መብት ሰጥቶታል። እ.አ.አ መስከረም 15 ቀን 2021 ኤሲ ሚላን በሻምፒዮንስ ሊጉ የ3 ለ 2 ሽንፈት ሲያስተናግድ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ግቡን አስቆጥሯል። በ2023 ኤሲ ሚላን ቶተንሃም ሆትስፐርስን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ 1 ለ 0 ሲያሽንፍ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 ሰኔ ወር ላይ ሪያል ማድሪድ ዲያዝ ከኤሲ ሚላን የሶስት ዓመታት የውሰት ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ መመለሱን አሳውቋል። ተጫዋቹ በኤሲ ሚላን ቆይታው 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ዲያዝ ወደ ሪያል ማድሪድ ከተመለሰ በኋላ ኮንትራቱን እስከ 2027 አራዝሟል። እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2023 ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ሪያል ማድሪድ ላስ ፓልማስን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል።   የክንፍ መስመር ተጫዋቹ ሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥ እና በአውሮፓ መድረክ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር እና ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ዲያዝ እስከ አሁን ለሪያል ማድሪድ ባደረጋቸው 129 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከነዚህም ውስጥ 13ቱ በላሊጋው ያስቆጠራቸው ናቸው። ከክለብ ወጣ ስንል የተጫዋቹን የብሔራዊ ቡድን ቆይታ እናገኛለን። ዲያዝ በታዳጊነቱ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ለስፔን ወጣት ቡድኖች ተጫውቷል። እ.አ.አ በ2016/17 የውድድር ዘመን ለስፔን ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ16 ዓመቱ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። በተለይም አዘርባጃን እ.አ.አ በ2017 ባዘጋጀችው 15ኛው የአውሮፓ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ላይ ያሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆት አስችሮታል። በዚያ ቀጥለው በነበሩ ዓመታትም ለስፔን ከ19 እና ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቷል። ብራሂም ዲያዝ በስፔን ታዳጊና ወጣት ቡድኖች ላይ በአጠቃላይ 28 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። የስፔን ታዋቂ የስፖርት ጋዜጣ ማርካ እ.አ.አ ጥር 23 ቀን 2023 ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን መጫወት ማቀዱን የሚመለከት ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ከዜግነቱ ጋር በተያያዘ ያሉ አንዳንድ የአስተደዳር ጉዳዮች በወቅቱ መፍትሄ አግኝተዋል። ይሁንና ኮትዲቯር እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሞሮኮው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከተጫዋቹ ጋር በተደረገ የቅድሚያ ስምምነት ለተጫዋቹ ጥሪ አልተደረገለትም። ዲያዝ እ.አ.አ መጋቢት 10 ቀን 2024 ለሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሀገሪቷ ብሔራዊ መጫወት እንደሚፈልግ በይፋ ማሳወቁን ማርካ በወቅቱ ዘግቧል። ጥያቄውም ተቀባይነት አገኘ። በወቅቱ የሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ብሔራዊ ቡድኑ ከአንጎላ እና ሞሪታኒያ ጋር ለነበረበት የወዳጅነት ጨዋታ ለዲያዝ ጥሪ አድርገውለታል። እ.አ.አ መጋቢት 22 ቀን 2024 ሞሮኮ አንጎላን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። እ.አ.አ ጥቅምት 6 ቀን 2024 ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከጋቦን ጋር ባደረገችው ጨዋታ 4 ለ 1 ስታሸንፍ የመጀመሪያ ግቡን ለሞሮኮ ማስቆጠር ቻለ። እ.አ.አ ሕዳር 15 ቀን 2024 ሞሮኮ በማጣሪያው ጋቦንን 5 ለ 1 ስትረታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። ከሶስት ቀናት በኋላ ሞሮኮ ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ 7 ለ 0 ስታሸንፍ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በሀገሩ ማልያ የመጀመሪያ ሀትሪኩን ሰርቷል። እ.አ.አ ጥቅምት 2025 ሞሮኮ ራባት ላይ ኮንጎ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 በማሸነፍ በስፔን ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተይዞ የነበረውን 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ክብረ ወሰን በመስበር ወደ 16 ማድረስ ችላለች። በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ ላይ ዲያዝ ተሰልፎ ተጫውቷል። የሞሮኮ ተከታታይ የማሸነፍ ጉዞ 19 ጨዋታዎች ደርሶ የነበረ ሲሆን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከማሊ ጋር አንድ አቻ ስትለያይ አብቅቷል።   ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማጣሪያ ብታልፍም አስቀድማ ውድድሩን እንድታዘጋጅ እድል አግኝታ የነበረው ጊኒ በዝግጅት ማነስ ምክንያት በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ከሁለት ዓመት በፊት አዘጋጅነቷ ተነጥቆ ለሞሮኮ ተሰጥቷል። ሞሮኮ የዘንድሮውን ውድድር በደማቅ ሁኔታ እያካሄደች ትገኛለች። በውድድሩ ላይ ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች መካከል ብራሂም ዲያዝ ተጠቃሽ ነው። በአፍሪካ ዋንጫው እስከ አሁን ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። በተሰለፈባቸው በእያንዳዱ ጨዋታዎች ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን በአምስት የአፍሪካ ዋንጫ ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ማሊን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሯል። ሀገሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜ እንድታልፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱንም እየመራ ይገኛል። ሞሮኮ በዚሁ ግስጋሴዋ ከቀጠለች ዲያዝ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና ኮከብ ተጫዋች የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜው ከናይጄሪያ ጋር ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ታደርጋለች። ዲያዝ በዚህ ጨዋታ ላይ ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ የእግር ኳስ ተንታኞች ብራሂም ዲያዝ እ.አ.አ በ2026 ወጥነት ያለው ብቃት ማሳየት ከቻለ የአፍሪካ ኮከብ ተጫዋችነት ሽልማቱን የሚወስድበት የለም እያሉ ይገኛሉ። ሞሮኳውያን በተጫዋቹ ፍቅር ልባቸው ከንፏል። በየጨዋታው ዲያዝ ዲያዝ እያሉ ከፍተኛ ድጋፍ እና ሙገሳ እየሰጡት ይገኛሉ። እሱም በድንቅ ብቃቱ ምላሽ እየሰጣቸው ነው። በተወለደበት ማላጋ ከተማ የጀመረው የእግር ኳስ ሕይወት በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የበለጠ አብቧል። የሞሮኮው አዲሱ ኮከብ ብራሂም ዲያዝ ቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወት በስኬት እና በድል የደመቀ እንደሚሆን ከአሁኑ ድንቅ ብቃቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም