ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የሊጉ መሪ አርሰናል ድል ሲቀናው ማንችስተር ሲቲ ነጥብ ጥሏል
Mar 4, 2026 55
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ29ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ ማምሻውን በመካሄድ ላይ ናቸው። በአሜክስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አርሰናል ቡካዮ ሳካ በዘጠነኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ጎል ብራይተንን 1 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል ነጥቡን ወደ 67 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ማንችስተር ሲቲ እና ኖቲንግሃም ፎረስት ሁለት አቻ ተለያይተዋል። በኢትሃድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አንቶዋን ሴሜንዮ እና ሮድሪ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሞርጋን ጊብስ-ዋይት እና ኤልዮት አንደርሰን ለፎረስት ጎሎቹን አሳርፈዋል። ማንችስተር ሲቲ በ60 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀራቸው ውሃ ሰማያዊዎቹ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያላቸው የነጥብ ልዩነት በነበረበት ወደ ሰባት ከፍ ብሏል። ሲቲ በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ነጥብ ጥሏል። ቼልሲ አስቶንቪላን ከሜዳው ውጪ 4 ለ 1 አሸንፏል። ጆአኦ ፔድሮ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል።ኮል ፓልመር ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ዳግላስ ሉዊስ ለአስቶንቪላ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ በ48 ነጥብ አምስተኛ፣ አስቶንቪላ በ51 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዘዋል። በሌላኛው ጨዋታ ዌስትሃም ዩናይትድ በክሪሴንሲዮ ሳመርቪል ጎል ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፏል።
የመንግሥታቱ ድርጅትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ ይገባል
Mar 4, 2026 107
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ እንደሚገባ ተገለጸ። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከጃፓን ኤምባሲ ጋር በመሆን የተባበሩት መንግሥታት ሪፎርም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል። የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ ቢሆኑም በተቋማዊ አወቃቀር ሥርዓት ላይ አፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ያገለሉ ናቸው። የአማኒ አፍሪካ ዳይሬክተር ሰለሞን አየለ ደርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት መዋቅር የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃ ሊወስድ ይገባል። በተቋማቱ የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥም ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ተከታታይ ሥራ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትና ከሌሎች ሀገራት ጋር ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን የዓለምአቀፍ ተቋማት ፍትሐዊ ውክልና ማስከበር የሚስችል መዋቅራዊ የሪፎርም እርምጃ እንዲወሰድ መስራት ይገባል ብለዋል። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በአፍሪካ ሕብረትና የአፍሪካ ዳያስፖራ ጉዳዮች ላይ በጥናትና ምርምር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የጋና አምባሳደር ሮበርት አፍሪይ(ዶ/ር)፤ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ያቀረበችው ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ችላ በመባሉ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ የሌላት ብቸኛ አህጉር አድርጓታል ብለዋል። ለዚህም የመንግስታቱ ድርጅት አፍሪካ በተሸከመችው የጸጥታው ምክር ቤት የሥራ ጫና ልክ ውክልና የሚያስገኛትን የሪፎርም እምርጃ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። በአፍሪካ ሕብረት የጃፓን ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኖቦሩ ሴኪጉቺ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በመንግስታቱ የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ላይ ፍትሐዊ ውክልና ሊሰጣት ይገባል ብለዋል። ጃፓንም አፍሪካ በመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የሚኖራትን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። ጃፓንና የጂ-4 አባል ሀገራት የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡም አስታውቀዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2024 በጸደቀው "የወደፊት ስምምነት" ላይ የጸጥታው ምክር ቤት መዋቅራዊ የማሻሻያ እርምጃ ለመወሰድ የተቀመጠው አቅጣጫ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የዳበረ አብሮነት የከተማዋን ምሳሌትነት እያደመቀ ነው
Mar 4, 2026 66
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በመተሳሰብ የዳበረ አብሮነት የከተማዋን ምሳሌትነት እያደመቀ እንደሚገኝ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የእስልምና እምነት ተከታዮች የኢፍጣር መርሐ-ግብር አክሂዷል። የአሥተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደ ከተማ አሥተዳደር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች በማስታወስ በጋራ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ማዘጋጀቱ ትልቅ ደስታ እንደሚሰጥ ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የእምነት ልዩነት ያልገደበው ተሳስቦና ተረዳድቶ በአንድነት የመኖር ጥበብ የከተማዋን ተምሳሌትነት እያደመቀ እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የኢፍጣር ሥነ-ሥርዓቱም የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር ያለውን ጠንካራ ትስስር በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም መሰል የመደጋገፍና መረዳዳት ዕሴቶች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል። በኢፍጣር መርሐ-ግብሩ ላይ የተሳተፉት የእምነቱ ተከታዮችም በከተማ አሥተዳደሩ ለተደረገላቸው ዝግጅት ምሥጋና አቅርበዋል።
ለምርጫ ስኬታማነት የዜጎች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው
Mar 4, 2026 83
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፡- ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የዜጎች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለጠቅላላ ምርጫው ያዘጋጀው "ምርጫች ነው - ሀገር ያለእኛ" ህብሬ ዜማ ማስመረቂያ መርኃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ምርጫው ስኬታማ የሚሆነው ዜጎች በንቃት ሲሳተፉ፣ ሲመዘገቡ እና ድምፃቸውን ሲሰጡ ነው ። በዚህም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ያላቸውን ተሳትፎ ለማነቃቃት፣ ለማበረታታት እና ለመቀስቀስ የመራጮች ትምህርት ጨምሮ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ ነው ብለዋል። በዛሬው ዕለት የተመረቀው ህብረ ዜማ ዜጎች በምርጫው ሂደት ያላቸውን ባለቤትነት እንዲረዱ እና ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ ለማነቃቃት፣ ለማበረታታት እና ለማነሳሳት የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። የጥበብ ሥራዎች ዜጎችን የማስተማር እና የማነቃቃት ትልቅ አቅም እንዳላቸው በመጥቀስ፤ ይህ የህብሬ ዜማም መልዕክቱ በቀላሉ ወደ ህዝቡ እንዲደርስ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። ቦርዱ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ገለልተኛ እና አካታች ለማድረግ የጀመረውን ዝግጅት አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል ። በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ የፊታችን ቅዳሜ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ የፌዴራል መንግሥት ለትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና የሕዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያለውን ጽኑ አቋም በግልጽ ያሳየ ነው - ስምረት ፓርቲ
Mar 4, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ጉዳይ የሰጡት ማብራሪያ የፌዴራል መንግሥት ለክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና የሕዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያለውን ጽኑ አቋም በግልጽ ያሳየ መሆኑን ስምረት ፓርቲ አስታወቀ። የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ወጣቱን ለዘመናት ተብትቦ ያቆየበት የተሳሳተ አመለካከት የተሰበረበትና እንደማያዋጣ ያስገነዘቡበት መሆኑ በክልሉ ተራማጅ ወጣቶችን ለመፍጠር ትልቅ እድል እንደሚሰጥ ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የትግራይ ሕዝብ ከጦርነት ይልቅ ሰላምና ልማት ይገባዋል ብለዋል። መንግሥት በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት ጽኑ ፍላጎት እንዳለውና ለዚህም ማንኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፈል አብራርተዋል። ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁም አሳስበዋል። በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረትም መንግሥት የባንክ፣ የኤሌትሪክ ኃይልና ቴሌኮም የመሳሰሉ አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲመለሱ ማድረጉን አስታውሰዋል። ይህን ተከትሎ የስምረት ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ ጣዕመ አርዓዶም ከኢዜአ ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማብራሪያ የሀገሪቷን ብሎም የትግራይ ክልልን ነባራዊና አሁናዊ ሁኔታን በግልጽ ያስቀመጠ ነው። ለትግራይ ክልል ልማትና ዕድገት ሰላምና መረጋጋት ወሳኝ ስለመሆኑ ጠንካራ መልዕክት የተላለፈበት ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግርኛ ቋንቋ የሰጡት ማብራሪያ የትግራይን ሕዝብ ያከበረ፣ ለሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ በመስጠት ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ለሕዝቡ ትልቅ እፎይታን የሚያጎናጽፍና ለዘላቂ ሁለንተናዊ እድገት ወሳኝ እንደሆነ ተናግረዋል። የክልሉ ሕዝብ ሲያነሳው ለቆየው የሰላም፣ የልማትና የእድገት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ መሆኑንም ነው ያመለከቱት። በተጨማሪም በትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን በኤርትራ በኩል የጽንፈኛው የሻዕቢያ ቡድን ሴራን በትክክለኛ መረጃ ላይ በመመስረት ያጋለጠ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሕዝቡን መጠቀሚያ በማድረግ የራሳቸውን ሴራና እኩይ ተግባር ለመፈጸም እየሠሩ ላሉ ሕገ ወጥ ቡድኖች ትልቅ መልዕክት የተላለፈበት ነው ያሉት ኃላፊው፤ ለሕዝቡ ሲባል መንግሥት ያሳየው ታጋሽነት ከፍተኛ መሆኑን ያመላከተ ነው ብለዋል። ይህም በትግራይ ሕዝብና በቀድሞ ሕወሓት ቡድን መካከል ሰፊ ልዩነት እንዳለ ጠቅሰው፤ መንግሥት ይህንን ባገናዘበ መልኩ ለሕዝብ ያለውን ወገንተኝነት በግልጽ ማሳየቱን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ የሰጡትን ምክረ ሐሳብ ጠንካራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህ ክልሉ ለወጣቶች በባለቤትነት የተሰጠ በመሆኑ ትልቅ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ወጣቱን ለዘመናት ተብትቦ ያቆየበት የተሳሳተ አመለካከት የተሰበረበትና እንደማያዋጣም ያስገነዘቡበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በክልሉ ተራማጅ ወጣት ለመፍጠር ትልቅ ዕድል እንደሚሰጥ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የትግራይ ወጣት ከቀድሞ ሕወሓት ቡድን ጋር የመሰለፍ ምንም ዓይነት ፍላጎት እንደሌለው በተለያዩ ሁኔታዎች እያሳየ መሆኑ ገልጸው፤ ወጣቱ ለአሮጌ አስተሳሰብ ራሱን አሳልፎ መስጠት እንደማይፈልግ አቋም አለው ነው ያሉት። የፌዴራል መንግሥት ለትግራይ ክልል ለልማት የመደበውን በጀት የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለጦርነት ዝግጅትና ለታጣቂዎች ቀለብ እያዋለ መሆኑን በግልጽ የተነተኑበት መንገድ የቡድኑን እኩይ ተግባር ያጋለጠ እውነታውን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የትግራይ ክልልን ጸጥታ በማደፍረስ ሥራ ላይ የተጠመደው የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለሕዝብ ጥቅም እና ልማት የሚመደብ በጀትን ለግል ጥቅማቸው በማዋል ሕዝቡን ለተባባሰ ችግርና መከራ ዳርጎታል ብለዋል። በተጨማሪም በክልሉ የመንግሥት ሠራተኞች ያለፍላጎታቸው ከደመወዛቸው ገንዘብ እየተቆረጠ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ሕዝቡን ተስፋ በማስቆረጥ ክልሉን ወደ ጦርነት ለማስገባት የሚደረግ ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለትግራይ ሕዝብ እጅግ ወቅታዊና ተጠባቂ ከመሆኑ ባሻገር ለክልሉ ሕዝብ ትልቅ እፎይታና እረፍት የሚሰጥ መሆኑን ነው የገለጹት። ከቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለመላቀቅ ጽኑ ፍላጎት ላለው የትግራይ ሕዝብ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ተስፋ የሚሰጥና ፊቱን ወደ ልማትና ብልፅግና እንዲያዞር እድል የሚፈጥር መሆኑንም አብራርተዋል።
ፖለቲካ
ለምርጫ ስኬታማነት የዜጎች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው
Mar 4, 2026 83
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፡- ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የዜጎች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለጠቅላላ ምርጫው ያዘጋጀው "ምርጫች ነው - ሀገር ያለእኛ" ህብሬ ዜማ ማስመረቂያ መርኃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ምርጫው ስኬታማ የሚሆነው ዜጎች በንቃት ሲሳተፉ፣ ሲመዘገቡ እና ድምፃቸውን ሲሰጡ ነው ። በዚህም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ያላቸውን ተሳትፎ ለማነቃቃት፣ ለማበረታታት እና ለመቀስቀስ የመራጮች ትምህርት ጨምሮ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ ነው ብለዋል። በዛሬው ዕለት የተመረቀው ህብረ ዜማ ዜጎች በምርጫው ሂደት ያላቸውን ባለቤትነት እንዲረዱ እና ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ ለማነቃቃት፣ ለማበረታታት እና ለማነሳሳት የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። የጥበብ ሥራዎች ዜጎችን የማስተማር እና የማነቃቃት ትልቅ አቅም እንዳላቸው በመጥቀስ፤ ይህ የህብሬ ዜማም መልዕክቱ በቀላሉ ወደ ህዝቡ እንዲደርስ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። ቦርዱ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ገለልተኛ እና አካታች ለማድረግ የጀመረውን ዝግጅት አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል ። በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ የፊታችን ቅዳሜ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ የፌዴራል መንግሥት ለትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና የሕዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያለውን ጽኑ አቋም በግልጽ ያሳየ ነው - ስምረት ፓርቲ
Mar 4, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ጉዳይ የሰጡት ማብራሪያ የፌዴራል መንግሥት ለክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና የሕዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያለውን ጽኑ አቋም በግልጽ ያሳየ መሆኑን ስምረት ፓርቲ አስታወቀ። የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ወጣቱን ለዘመናት ተብትቦ ያቆየበት የተሳሳተ አመለካከት የተሰበረበትና እንደማያዋጣ ያስገነዘቡበት መሆኑ በክልሉ ተራማጅ ወጣቶችን ለመፍጠር ትልቅ እድል እንደሚሰጥ ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የትግራይ ሕዝብ ከጦርነት ይልቅ ሰላምና ልማት ይገባዋል ብለዋል። መንግሥት በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት ጽኑ ፍላጎት እንዳለውና ለዚህም ማንኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፈል አብራርተዋል። ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁም አሳስበዋል። በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረትም መንግሥት የባንክ፣ የኤሌትሪክ ኃይልና ቴሌኮም የመሳሰሉ አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲመለሱ ማድረጉን አስታውሰዋል። ይህን ተከትሎ የስምረት ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ ጣዕመ አርዓዶም ከኢዜአ ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማብራሪያ የሀገሪቷን ብሎም የትግራይ ክልልን ነባራዊና አሁናዊ ሁኔታን በግልጽ ያስቀመጠ ነው። ለትግራይ ክልል ልማትና ዕድገት ሰላምና መረጋጋት ወሳኝ ስለመሆኑ ጠንካራ መልዕክት የተላለፈበት ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግርኛ ቋንቋ የሰጡት ማብራሪያ የትግራይን ሕዝብ ያከበረ፣ ለሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ በመስጠት ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ለሕዝቡ ትልቅ እፎይታን የሚያጎናጽፍና ለዘላቂ ሁለንተናዊ እድገት ወሳኝ እንደሆነ ተናግረዋል። የክልሉ ሕዝብ ሲያነሳው ለቆየው የሰላም፣ የልማትና የእድገት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ መሆኑንም ነው ያመለከቱት። በተጨማሪም በትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን በኤርትራ በኩል የጽንፈኛው የሻዕቢያ ቡድን ሴራን በትክክለኛ መረጃ ላይ በመመስረት ያጋለጠ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሕዝቡን መጠቀሚያ በማድረግ የራሳቸውን ሴራና እኩይ ተግባር ለመፈጸም እየሠሩ ላሉ ሕገ ወጥ ቡድኖች ትልቅ መልዕክት የተላለፈበት ነው ያሉት ኃላፊው፤ ለሕዝቡ ሲባል መንግሥት ያሳየው ታጋሽነት ከፍተኛ መሆኑን ያመላከተ ነው ብለዋል። ይህም በትግራይ ሕዝብና በቀድሞ ሕወሓት ቡድን መካከል ሰፊ ልዩነት እንዳለ ጠቅሰው፤ መንግሥት ይህንን ባገናዘበ መልኩ ለሕዝብ ያለውን ወገንተኝነት በግልጽ ማሳየቱን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ የሰጡትን ምክረ ሐሳብ ጠንካራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህ ክልሉ ለወጣቶች በባለቤትነት የተሰጠ በመሆኑ ትልቅ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ወጣቱን ለዘመናት ተብትቦ ያቆየበት የተሳሳተ አመለካከት የተሰበረበትና እንደማያዋጣም ያስገነዘቡበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በክልሉ ተራማጅ ወጣት ለመፍጠር ትልቅ ዕድል እንደሚሰጥ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የትግራይ ወጣት ከቀድሞ ሕወሓት ቡድን ጋር የመሰለፍ ምንም ዓይነት ፍላጎት እንደሌለው በተለያዩ ሁኔታዎች እያሳየ መሆኑ ገልጸው፤ ወጣቱ ለአሮጌ አስተሳሰብ ራሱን አሳልፎ መስጠት እንደማይፈልግ አቋም አለው ነው ያሉት። የፌዴራል መንግሥት ለትግራይ ክልል ለልማት የመደበውን በጀት የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለጦርነት ዝግጅትና ለታጣቂዎች ቀለብ እያዋለ መሆኑን በግልጽ የተነተኑበት መንገድ የቡድኑን እኩይ ተግባር ያጋለጠ እውነታውን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የትግራይ ክልልን ጸጥታ በማደፍረስ ሥራ ላይ የተጠመደው የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለሕዝብ ጥቅም እና ልማት የሚመደብ በጀትን ለግል ጥቅማቸው በማዋል ሕዝቡን ለተባባሰ ችግርና መከራ ዳርጎታል ብለዋል። በተጨማሪም በክልሉ የመንግሥት ሠራተኞች ያለፍላጎታቸው ከደመወዛቸው ገንዘብ እየተቆረጠ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ሕዝቡን ተስፋ በማስቆረጥ ክልሉን ወደ ጦርነት ለማስገባት የሚደረግ ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለትግራይ ሕዝብ እጅግ ወቅታዊና ተጠባቂ ከመሆኑ ባሻገር ለክልሉ ሕዝብ ትልቅ እፎይታና እረፍት የሚሰጥ መሆኑን ነው የገለጹት። ከቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለመላቀቅ ጽኑ ፍላጎት ላለው የትግራይ ሕዝብ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ተስፋ የሚሰጥና ፊቱን ወደ ልማትና ብልፅግና እንዲያዞር እድል የሚፈጥር መሆኑንም አብራርተዋል።
ተዓማኒነት ያላቸውን መረጃዎች በማጋራት የኢትዮጵያን የብሔራዊ ደኅንነት አጀንዳዎች ማሳካት ከዜጎች ይጠበቃል
Mar 4, 2026 104
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፡- ዜጎች ተዓማኒነት ያላቸውና ተጨባጭ መረጃዎችን በማጋራት የኢትዮጵያን የብሔራዊ ደኅንነት አጀንዳዎች ለማሳካት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጠየቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከኅብረተሰቡ መረጃ የሚቀበልበትና ሌሎችም የተለያዩ አገልግሎቶች የሚሰጥ የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርም ይፋ አድርጓል። አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳመለከተው፤ በተቋሙ የውስጥ ዐቅም የበለፀገው ከመደበኛው ድረ-ገጽ በብዙ ገፅታዎቹ የሚለየው የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርም ዜጎች በፀጥታ፣ በደኅንነትና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ከየትኛውም ስፍራ ሆነው መረጃ የሚሰጡበት የሪፖርት ማድረጊያ ክፍል አለው፡፡ ሀገራዊ የደኅንነት፣ የመረጃና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተም ወቅታዊ መረጃዎችን ያጋራል ነው የተባለው። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እንዳሉት፤ የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርሙ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚያጋጥም የስጋት ተጋላጭነትን የተመለከቱ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎች የሚሰጥ ነው። ኅብረተሰቡም ሆነ የውጭ ዜጎች መረጃውን በመጠቀም በየትኛውም ስፍራ ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በማገዝ ከፍተኛ ሚና ያበረክታል ነው ያሉት። የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርሙ ለወደፊቱ የተቋሙን መስፈርት የሚያሟሉና ልዩ ተሰጥዖ ያላቸው ዜጎች አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን በመቀላቀል ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ የሚያስችል የማመልከቻ ገጽ የተካተተበት መሆኑንም አስታውቀዋል። ፕላትፎርሙ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ እያከናወነ በሚገኘው ሪፎርም ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ በማበልፀግ የላቀ የመፈፀም ዐቅም ያለው ተቋም ለመገንባት የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑም ተጠቁሟል። ዜጎችም ተዓማኒነት ያላቸውና ተጨባጭ መረጃዎችን በማጋራት የኢትዮጵያን የብሔራዊ ደኅንነት አጀንዳዎች ለማሳካት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ተጠይቀዋል። የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርሙ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የደኅንነት ተጋላጭነት ፍተሻ ተደርጎለት የማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እንደተሰጠው ተመላክቷል።
ሀገራዊ ለውጡ የሴቶች የፖለቲካ ውክልናና የውሳኔ ሰጪነት አቅምን በተግባር አረጋግጧል
Mar 4, 2026 112
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ለውጡ የሴቶች የፖለቲካ ውክልናና የውሳኔ ሰጪነት አቅምን በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን የሴቶች አደረጃጀቶች ገለፁ። በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ሳሚያ አብደላ እንዳሉት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃም ሆነ በኦሮሚያ ክልል ለሴቶች ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም ሆነ በክልሉ የሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎና የውሳኔ ሰጪነት ሚና በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን ጠቁመው፣ ይህም ለለውጡ ስኬት ትልቅ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። የሴቶች በኢኮኖሚው ዘርፍ ያላቸው ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን ያነሱት ወይዘሮ ሳሚያ ይህም ምርታማነታቸውን በማሳደግ ረገድ የጎላ ድርሻ እንዳለውና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጠ መሆኑን አስረድተዋል። በትምህርት፣ በጤናና በሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራትን ይበልጥ ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ንቁ ተሳታፊ በመሆን የዲሞክራሲ ግንባታ ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ብሩክ ባልቻ በበኩላቸው ሴቶች ለኢትዮጵያ ብልፅግና መረጋገጥ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ልማትን ለማረጋገጥ የሴቶች ድርሻ ጉልህ እንደሆነ ጠቁመው ሴቶች በፖለቲካ ያላቸው ተሳትፎ እያደገ በመምጣቱ ለሀገር አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆናቸውን ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ እያደገ መሆኑን የገለፁት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ፀደኒያ ግርማይ ናቸው። የለውጡ ዓመታት የሴቶች የውሳኔ ሰጪነት በተግባር እየተረጋገጠ የመጣበት እንደሆነም ነው ያስረዱት። የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንት መስከረም አበበ በበኩላቸው ሴቶች ህብረ ብሄራዊ ሀገር ለመገንባትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶችን ፖለቲካዊ ተሳትፎ በተግባር የሚያረጋግጡ ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀው በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ከሴቶች አደረጃጀትና ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለአንድ ወር ያህል የዘለቀ ሀገራዊ የንቅናቄ መድረክ 10 ሚሊየን በላይ ሴቶችን ማወያየት መቻሉን ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያን የሚገነባት እና የሚያጸናት የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ
Mar 4, 2026 117
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ ለሀገራዊ መግባባት በምክክሩ የሚያደርገውን አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል። ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 የተቋቋመው፣ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ መሠረታዊ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት እና በሕዝቦች መካከል የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ነው። ኮሚሽኑ አካታች የሆኑ የምክክር መድረኮችን በማመቻቸት ለዘላቂ ሰላም እና ለጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚረዱ ምክረ ሀሳቦችን የማቅረብ ግብም አለው። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥ በየክልሎቹና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተወካዮች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎችን በስፋት አከናውኗል። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ብልፅግና ፓርቲ ምክክር ኢትዮጵያን ጠንካራ ሀገር ያደርጋታል የሚል ፅኑ እምነት እንዳለው ገልፀዋል። ብልፅግና ፓርቲ በሀገራዊ ምክክር የእስካሁን ሂደት ውስጥ ግልፅ የሆነ አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መቆየቱንም አስታውሰዋል። የምክክር ሂደት ለዘመናት የተሻገረና ከሀገረ መንግስት ግንባታ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በዘመናት መካከል በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው ያሉት አቶ መለሰ፤ ፓርቲው ምክክርን የአንድ ወገን ሥራ አድርጎ እንደማይመለከተውም ተናግረዋል። ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ መሆኑን በማመን፣ ፓርቲው በውይይት በመሳተፍና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ይበጃሉ ያላቸውን አጀንዳዎች በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እንደ ገዥ ፓርቲም ሂደቱ እንዲሳካ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን አክለዋል። የምክክር ሂደቱ ለስምንት ወራት መራዘሙ ኮሚሽኑ ሥራውን በአግባቡና በጥራት እንዲያጠናቅቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ብልፅግና ፓርቲም በቀጣይ ወራት ለሀገራዊ መግባባት እየተካሄደ ላለው ምክክር አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በዚህም ፓርቲው ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ የመግባባት ደረጃ ላይ እንድትደርስ ይሰራል ብለዋል። ብልፅግና ፓርቲ የምክክር ሂደት ለትውልድ የሚኖረውን የላቀ ፋይዳ በሚገባ የሚገነዘብ በመሆኑ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሁሌም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በትግሪኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ካስተላለፏቸው መልዕክቶች
Mar 3, 2026 155
ለትግራይ ሕዝብና ወጣቶች ያስተላለፉት መልዕክት፡- "የትግራይ ሕዝብ ከጦርነት ይልቅ ሰላምና ልማት ይገባዋል" ብለዋል። ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ መክረዋል። መንግሥት በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት ጽኑ ፍላጎት እንዳለውና ለዚህም ማንኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል አረጋግጠዋል። የሰሜኑን ጦርነት መንስኤዎች በተመለከተ ህወሓት ከ50 ዓመት በፊት በነበረ ኋላቀር አስተሳሰብ የታሰረ መሆኑና ለውጥን ለመቀበል አለመፈለጉ። ዓለም በቴክኖሎጂና በ"ፕራግማቲዝም" በምትመራበት ዘመን፣ ድርጅቱ በአሮጌው መንገድ ለመጓዝ መሞከሩ ለግጭት ዳርጎታል። ቆሞ ቀሩ ኃይል "ኢትዮጵያ ትፈርሳለች" የሚል የተሳሳተ ስጋት በመዝራት የለውጡን ኃይል እንደ ጠላት ማየቱ። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊነት በተመለከተ ፡- መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ሰላም እንዲያገኝ ባንክ፣ መብራትና ቴሌኮም የመሳሰሉ አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲመለሱ ማድረጉን ገልጸዋል። ሆኖም ቆሞ ቀሩ ቡድን ስምምነቱን "መርጦ የመተግበር" ዝንባሌ እያሳየ መሆኑን ተችተዋል። በተለይም ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ውሳኔ አለማክበሩን ጠቅሰዋል። ድርጅቱ ለልማት የተመደበውን በጀት ለጦርነት ዝግጅትና ለታጣቂዎች ቀለብ እየዋለ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም በትግራይ ሕዝብ ላይ ተጨማሪ መከራ እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በጦርነቱ ወቅት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ፡- ጦርነት ሁልጊዜም አስከፊ ገጽታ እንዳለው ገልጸው፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሽግግር ፍትሕ (Transitional Justice) አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ ሂደት ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ በሆነ መንገድ ሊካሄድ እንደሚገባውና ወንጀል የፈጸሙ አካላት በሕግ መጠየቅ እንዳለባቸው ገልጸዋል። የኤርትራ መንግሥት (ሻዕቢያ) ሚና በጦርነቱ ወቅት የኤርትራ ጦር ያደረገው ድጋፍ የሚታወስ መሆኑን ጠቅሰዋል። ሆኖም በጦርነቱ ሂደት የተፈጸሙ ማናቸውም ዓይነት ጥፋቶች፣ ግድያዎችና ዘረፋዎች (በተለይም በአክሱም፣ ዓድዋና ሽሬ አካባቢዎች) የማይቀበሉትና የሚወገዝ ተግባር መሆኑን በግልጽ አስታውቀዋል። መንግሥት ማንኛውንም የውጭ ኃይል ጣልቃ ገብነት እንደሚቃወምና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር እንደሚሠራ ገልጸዋል።
የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤን የማስቀጠል አባዜ ምክንያት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Mar 3, 2026 125
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው የህወሓት አመራር ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤ የማስቀጠል አባዜ ምክንያት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ቆይታ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የሰሜኑ ጦርነት መነሻ ምክንያቶችን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፤ ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና እኔ ብቻ በሚል ስሜት በመዋጡ ግጭት እንዲነሳ መንስኤ መሆኑን ገልጸዋል። ህወሓት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብ የታሠረ ድርጅት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ብቻ ሳይሆን ዓይኑን ጨፍኖ ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ ርምጃዎችን ሲወስድ መቆየቱንም ተናግረዋል። የለውጡ ኃይል የጀመረውን ጉዞ ለማደናቀፍ መሞከሩን ገልጸው፤ በህወሓት ቆሞ ቀር አስተሳሰብ የተነሳው ጦርነት ጉዳት ማስከተሉንም አንስተዋል። ሁለተኛው ቁልፍ ምክንያት ደግሞ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ ጋር የተሣሠረ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ህወሓት ኢትዮጵያ በጥርጣሬና በሥጋት ውስጥ እንድትኖር መስራቱ ለችግሮች መባባስ ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል። ቆሞ ቀሩ ኃይል ከ50 ዓመት በፊት ከነበረው አስተሳሰብ ውጭ ሊንቀሳቀስ አለመቻሉን ጠቅሰው፤ ይህ ደግሞ ከለውጡ ጋር አብሮ ለመሄድ እንዳላስቻለው ገልጸዋል። የለውጥ ኃይሉ ዓለምን ያስደመመ ተአምራዊ ለውጦችን ማምጣቱን ጠቅሰው፤ ቆሞ ቀር ኃይሉ ከለውጥ ኃይሉ ጋር ተስማምቶ ሕዝቡንና ነፍሱን እንደመለወጥ የልማት ሽታ ከማያውቁ ኋላቀሮች ጋር እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ ያለው የፖለቲካ ስብራት ሌላኛው መንስኤ እንደሆነ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተሳሳተ ትርክት ላይ የተመሰረተው ፖለቲካዊ መዋቅር የፖለቲካ ስርዓቱ እንዲበላሽ ማድረጉን ነው ያብራሩት። ጦርነቱ የራሱ ልዩ ገጽታዎች እንዳሉት ሆኖ ከሀገራዊ መዋቅር ችግር የተለየ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባውም ብለዋል። ይህ አዙሪት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መሰበር አለበት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይሄንን ለመስበር ደግሞ ኃላፊነት መውሰድ እንደሚገባ ገልጸዋል። እንደ ትውልድ ይበቃል ብለን መሥራት አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የመንግስት አቋም ችግሮችን በውይይት መፍታት አማራጭ የሌለው መንገድ እንደሆነ በጽኑ እንደሚያምንም ገልጸዋል። ይሄንን ለማድረግ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ወሳኝ ሀገራዊ መፍትሔ ሊሆን ይችላል ብለን እናምናለን ብለዋል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ እስካሁን ከሞላ ጎደል ከትግራይ ውጭ አብዛኛው ሥራ እየተገባደደ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በትግራይ ክልል ግን ውይይት እንዳይደረግ፣ ሕዝባችን ቁጭ ብሎ እንዳይወያይ፣ ጥያቄ አንሥቶ መፍትሔ እንዳያገኝ፣ ያ ቆሞ ቀር ኃይል ሆን ብሎ እየሠራ ይገኛል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ደግሞ ትክክለኛ አካሄድ ነው ብዬ አላምንም ብለዋል።
ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል
Mar 3, 2026 139
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት መቻሉን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። ዛሬ "የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግሥት ግንባታ!" በሚል መሪ ሀሳብ በዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት ቅንጅት ላይ የሚያተኩር ሀገራዊ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት የፍርድ ቤቶች የለውጥ ተግባራትን አስመልክቶ ባቀረቡት የመነሻ ሐሳብ፤ የዳኝነት ነጻነትን ለማጠናከር የሕግ ማሻሻያ መደረጉን ተናግረዋል። ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አኳያም ግልጽ ችሎትን የማስፋፋት ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፤ ግልጽ ችሎት ከነበረበት 65 በመቶ ወደ 91 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። ፍርድ ቤቶች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ድምፅን ወደ ጽሁፍ የሚቀይር ቴክኖሎጂን በመጠቀም ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ኮሚሽኑ እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እስካሁን ውጤታማ የሚባሉ ሥራዎችን ሰርቷል ብለዋል። የሀገሪቱን ሁሉንም ክልሎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ 93 በመቶ ማካተት መቻሉን ጠቁመው፤ በቀጣይም አጀንዳ መቅረጽና ይፋ ማድረግ እንዲሁም ሀገራዊ ምክክር ማካሄድ ከሚከናወኑ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ የቦርዱን የለውጥ እና ቀጣይ ተግባራት ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ቦርዱ ባለፉት ዓመታት ተቋማዊ የሕግ ማሻሻያዎችን በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዕጩዎችን ምዝገባ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል በማከናወን ማጠናቀቅ መቻሉን ተናግረው፤ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስልጠና መሰጠት መቻሉንም ገልጸዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬታማነት ለማከናወን "ምርጫዬ" የመራጮች መመዝገቢያ የዲጂታል አማራጭ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ፤ ነጻና ገለልተኛ ተቋም ለመገንባት የአዋጅ ማሻሻያ፣ ደንብና መመሪያዎችን ማሻሻል መቻሉን ገልጸዋል። ከኦዲት ሽፋን አኳያም የፋይናንሻል ኦዲት መቶ በመቶ ማከናወን መቻሉን በመጥቀስ፤ የክዋኔ ኦዲትንም ከ24 ወደ 41 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል። የኢትየጵያ ሕዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ከለውጡ ወዲህ በተከናወኑ የለውጥ ስራዎችም ከአሰራርና ከሰው ሃይል አኳያ፣ የሕግ ማሻሻያ ተግባራት፣ ከቴክኖሎጂ አኳያ እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራሮች ተዘርግተው ስኬታማ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ከቴክኖሎጂ ስራዎች ለግልጸኝነት፣ ለተጠያቂነት፣ ለቅልጥፍና እንዲሁም ለውጤታማነት ምቹ መደላድል መፍጠራቸውን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ፤ ከለውጡ በፊት ኮሚሽኑ ገለልተኛ እና ውጤታማ ያልነበረ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ምቹ የሕግ ማዕቀፍ፣ አዲስ የሰው ሃብት መዋቅር፣ ብቃትና አቅም ያለው አመራር መፍጠር፣ ሥራን የሚያቀላጥፉ በቴክኖሎጂ የተደገፉ መፍትሔዎች፣ የመረጃ ስርዓት በቴክኖሎጂ የሚመራ መደረጉ እንዲሁም የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ መቻሉን ጠቁመዋል። የመድረኩ ታሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉን አድንቀዋል፡፡ ይህም ለሀገረ መንግስት ግንባታ ብሎም ለዘላቂ ልማትና ለሕዝቦች ተጠቃሚነት መረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በሰጡት ማጠቃለያ፤ ለምክር ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት በሕግ የተሰጣቸውን ሥልጣንና ኃላፊነት በገለልተኝነትና በነፃነት እየተወጡ ይገኛሉ። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዳኝነትና ዲሞክራሲ ተቋማት ላይ መሠረታዊ የሪፎርም ሥራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። ተቋማቱ ላይ ከተከናወኑ የለውጡ ስራዎች መካከል የማቋቋሚያ አዋጆቻቸውን በድጋሚ መፈተሽና ማሻሻል፣ የአመራር ሥርዓታቸውን ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ፣ ዘመናዊና ግልጽነት ያለው የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት መቻል ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል፡፡ የተቋማት ግንባታ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ነው ያሉት አፈ-ጉባኤው፤ ተቋማቱ ነፃ ሆነው እንዲሠሩ መደረጉ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ዴሞክራሲን እውን ለማድረግ ትልቅ መሠረት እንደሚጥል አጽንኦት ሰጥተዋል። ተቋማቱ በገለልተኝነት መሥራታቸው ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን ለማፋጠን ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ጠቁመዋል።
ፖለቲካ
ለምርጫ ስኬታማነት የዜጎች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው
Mar 4, 2026 83
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፡- ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የዜጎች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለጠቅላላ ምርጫው ያዘጋጀው "ምርጫች ነው - ሀገር ያለእኛ" ህብሬ ዜማ ማስመረቂያ መርኃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ምርጫው ስኬታማ የሚሆነው ዜጎች በንቃት ሲሳተፉ፣ ሲመዘገቡ እና ድምፃቸውን ሲሰጡ ነው ። በዚህም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ያላቸውን ተሳትፎ ለማነቃቃት፣ ለማበረታታት እና ለመቀስቀስ የመራጮች ትምህርት ጨምሮ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ ነው ብለዋል። በዛሬው ዕለት የተመረቀው ህብረ ዜማ ዜጎች በምርጫው ሂደት ያላቸውን ባለቤትነት እንዲረዱ እና ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ ለማነቃቃት፣ ለማበረታታት እና ለማነሳሳት የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። የጥበብ ሥራዎች ዜጎችን የማስተማር እና የማነቃቃት ትልቅ አቅም እንዳላቸው በመጥቀስ፤ ይህ የህብሬ ዜማም መልዕክቱ በቀላሉ ወደ ህዝቡ እንዲደርስ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። ቦርዱ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ገለልተኛ እና አካታች ለማድረግ የጀመረውን ዝግጅት አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል ። በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ የፊታችን ቅዳሜ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ የፌዴራል መንግሥት ለትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና የሕዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያለውን ጽኑ አቋም በግልጽ ያሳየ ነው - ስምረት ፓርቲ
Mar 4, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ጉዳይ የሰጡት ማብራሪያ የፌዴራል መንግሥት ለክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና የሕዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያለውን ጽኑ አቋም በግልጽ ያሳየ መሆኑን ስምረት ፓርቲ አስታወቀ። የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ወጣቱን ለዘመናት ተብትቦ ያቆየበት የተሳሳተ አመለካከት የተሰበረበትና እንደማያዋጣ ያስገነዘቡበት መሆኑ በክልሉ ተራማጅ ወጣቶችን ለመፍጠር ትልቅ እድል እንደሚሰጥ ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የትግራይ ሕዝብ ከጦርነት ይልቅ ሰላምና ልማት ይገባዋል ብለዋል። መንግሥት በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት ጽኑ ፍላጎት እንዳለውና ለዚህም ማንኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፈል አብራርተዋል። ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁም አሳስበዋል። በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረትም መንግሥት የባንክ፣ የኤሌትሪክ ኃይልና ቴሌኮም የመሳሰሉ አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲመለሱ ማድረጉን አስታውሰዋል። ይህን ተከትሎ የስምረት ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ ጣዕመ አርዓዶም ከኢዜአ ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማብራሪያ የሀገሪቷን ብሎም የትግራይ ክልልን ነባራዊና አሁናዊ ሁኔታን በግልጽ ያስቀመጠ ነው። ለትግራይ ክልል ልማትና ዕድገት ሰላምና መረጋጋት ወሳኝ ስለመሆኑ ጠንካራ መልዕክት የተላለፈበት ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግርኛ ቋንቋ የሰጡት ማብራሪያ የትግራይን ሕዝብ ያከበረ፣ ለሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ በመስጠት ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ለሕዝቡ ትልቅ እፎይታን የሚያጎናጽፍና ለዘላቂ ሁለንተናዊ እድገት ወሳኝ እንደሆነ ተናግረዋል። የክልሉ ሕዝብ ሲያነሳው ለቆየው የሰላም፣ የልማትና የእድገት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ መሆኑንም ነው ያመለከቱት። በተጨማሪም በትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን በኤርትራ በኩል የጽንፈኛው የሻዕቢያ ቡድን ሴራን በትክክለኛ መረጃ ላይ በመመስረት ያጋለጠ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሕዝቡን መጠቀሚያ በማድረግ የራሳቸውን ሴራና እኩይ ተግባር ለመፈጸም እየሠሩ ላሉ ሕገ ወጥ ቡድኖች ትልቅ መልዕክት የተላለፈበት ነው ያሉት ኃላፊው፤ ለሕዝቡ ሲባል መንግሥት ያሳየው ታጋሽነት ከፍተኛ መሆኑን ያመላከተ ነው ብለዋል። ይህም በትግራይ ሕዝብና በቀድሞ ሕወሓት ቡድን መካከል ሰፊ ልዩነት እንዳለ ጠቅሰው፤ መንግሥት ይህንን ባገናዘበ መልኩ ለሕዝብ ያለውን ወገንተኝነት በግልጽ ማሳየቱን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ የሰጡትን ምክረ ሐሳብ ጠንካራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህ ክልሉ ለወጣቶች በባለቤትነት የተሰጠ በመሆኑ ትልቅ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ወጣቱን ለዘመናት ተብትቦ ያቆየበት የተሳሳተ አመለካከት የተሰበረበትና እንደማያዋጣም ያስገነዘቡበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በክልሉ ተራማጅ ወጣት ለመፍጠር ትልቅ ዕድል እንደሚሰጥ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የትግራይ ወጣት ከቀድሞ ሕወሓት ቡድን ጋር የመሰለፍ ምንም ዓይነት ፍላጎት እንደሌለው በተለያዩ ሁኔታዎች እያሳየ መሆኑ ገልጸው፤ ወጣቱ ለአሮጌ አስተሳሰብ ራሱን አሳልፎ መስጠት እንደማይፈልግ አቋም አለው ነው ያሉት። የፌዴራል መንግሥት ለትግራይ ክልል ለልማት የመደበውን በጀት የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለጦርነት ዝግጅትና ለታጣቂዎች ቀለብ እያዋለ መሆኑን በግልጽ የተነተኑበት መንገድ የቡድኑን እኩይ ተግባር ያጋለጠ እውነታውን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የትግራይ ክልልን ጸጥታ በማደፍረስ ሥራ ላይ የተጠመደው የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለሕዝብ ጥቅም እና ልማት የሚመደብ በጀትን ለግል ጥቅማቸው በማዋል ሕዝቡን ለተባባሰ ችግርና መከራ ዳርጎታል ብለዋል። በተጨማሪም በክልሉ የመንግሥት ሠራተኞች ያለፍላጎታቸው ከደመወዛቸው ገንዘብ እየተቆረጠ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ሕዝቡን ተስፋ በማስቆረጥ ክልሉን ወደ ጦርነት ለማስገባት የሚደረግ ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለትግራይ ሕዝብ እጅግ ወቅታዊና ተጠባቂ ከመሆኑ ባሻገር ለክልሉ ሕዝብ ትልቅ እፎይታና እረፍት የሚሰጥ መሆኑን ነው የገለጹት። ከቀድሞ ሕወሓት ቡድን ለመላቀቅ ጽኑ ፍላጎት ላለው የትግራይ ሕዝብ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ተስፋ የሚሰጥና ፊቱን ወደ ልማትና ብልፅግና እንዲያዞር እድል የሚፈጥር መሆኑንም አብራርተዋል።
ተዓማኒነት ያላቸውን መረጃዎች በማጋራት የኢትዮጵያን የብሔራዊ ደኅንነት አጀንዳዎች ማሳካት ከዜጎች ይጠበቃል
Mar 4, 2026 104
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፡- ዜጎች ተዓማኒነት ያላቸውና ተጨባጭ መረጃዎችን በማጋራት የኢትዮጵያን የብሔራዊ ደኅንነት አጀንዳዎች ለማሳካት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጠየቀ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከኅብረተሰቡ መረጃ የሚቀበልበትና ሌሎችም የተለያዩ አገልግሎቶች የሚሰጥ የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርም ይፋ አድርጓል። አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳመለከተው፤ በተቋሙ የውስጥ ዐቅም የበለፀገው ከመደበኛው ድረ-ገጽ በብዙ ገፅታዎቹ የሚለየው የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርም ዜጎች በፀጥታ፣ በደኅንነትና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ከየትኛውም ስፍራ ሆነው መረጃ የሚሰጡበት የሪፖርት ማድረጊያ ክፍል አለው፡፡ ሀገራዊ የደኅንነት፣ የመረጃና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተም ወቅታዊ መረጃዎችን ያጋራል ነው የተባለው። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እንዳሉት፤ የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርሙ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚያጋጥም የስጋት ተጋላጭነትን የተመለከቱ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎች የሚሰጥ ነው። ኅብረተሰቡም ሆነ የውጭ ዜጎች መረጃውን በመጠቀም በየትኛውም ስፍራ ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በማገዝ ከፍተኛ ሚና ያበረክታል ነው ያሉት። የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርሙ ለወደፊቱ የተቋሙን መስፈርት የሚያሟሉና ልዩ ተሰጥዖ ያላቸው ዜጎች አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን በመቀላቀል ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ የሚያስችል የማመልከቻ ገጽ የተካተተበት መሆኑንም አስታውቀዋል። ፕላትፎርሙ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ እያከናወነ በሚገኘው ሪፎርም ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ በማበልፀግ የላቀ የመፈፀም ዐቅም ያለው ተቋም ለመገንባት የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑም ተጠቁሟል። ዜጎችም ተዓማኒነት ያላቸውና ተጨባጭ መረጃዎችን በማጋራት የኢትዮጵያን የብሔራዊ ደኅንነት አጀንዳዎች ለማሳካት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ተጠይቀዋል። የኮሙኒኬሽን ፕላትፎርሙ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የደኅንነት ተጋላጭነት ፍተሻ ተደርጎለት የማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እንደተሰጠው ተመላክቷል።
ሀገራዊ ለውጡ የሴቶች የፖለቲካ ውክልናና የውሳኔ ሰጪነት አቅምን በተግባር አረጋግጧል
Mar 4, 2026 112
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ለውጡ የሴቶች የፖለቲካ ውክልናና የውሳኔ ሰጪነት አቅምን በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን የሴቶች አደረጃጀቶች ገለፁ። በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ሳሚያ አብደላ እንዳሉት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃም ሆነ በኦሮሚያ ክልል ለሴቶች ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም ሆነ በክልሉ የሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎና የውሳኔ ሰጪነት ሚና በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን ጠቁመው፣ ይህም ለለውጡ ስኬት ትልቅ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። የሴቶች በኢኮኖሚው ዘርፍ ያላቸው ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን ያነሱት ወይዘሮ ሳሚያ ይህም ምርታማነታቸውን በማሳደግ ረገድ የጎላ ድርሻ እንዳለውና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጠ መሆኑን አስረድተዋል። በትምህርት፣ በጤናና በሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራትን ይበልጥ ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ንቁ ተሳታፊ በመሆን የዲሞክራሲ ግንባታ ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ብሩክ ባልቻ በበኩላቸው ሴቶች ለኢትዮጵያ ብልፅግና መረጋገጥ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ልማትን ለማረጋገጥ የሴቶች ድርሻ ጉልህ እንደሆነ ጠቁመው ሴቶች በፖለቲካ ያላቸው ተሳትፎ እያደገ በመምጣቱ ለሀገር አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆናቸውን ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ እያደገ መሆኑን የገለፁት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ፀደኒያ ግርማይ ናቸው። የለውጡ ዓመታት የሴቶች የውሳኔ ሰጪነት በተግባር እየተረጋገጠ የመጣበት እንደሆነም ነው ያስረዱት። የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንት መስከረም አበበ በበኩላቸው ሴቶች ህብረ ብሄራዊ ሀገር ለመገንባትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶችን ፖለቲካዊ ተሳትፎ በተግባር የሚያረጋግጡ ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀው በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ከሴቶች አደረጃጀትና ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለአንድ ወር ያህል የዘለቀ ሀገራዊ የንቅናቄ መድረክ 10 ሚሊየን በላይ ሴቶችን ማወያየት መቻሉን ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያን የሚገነባት እና የሚያጸናት የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ
Mar 4, 2026 117
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ ለሀገራዊ መግባባት በምክክሩ የሚያደርገውን አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል። ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 የተቋቋመው፣ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ መሠረታዊ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት እና በሕዝቦች መካከል የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ነው። ኮሚሽኑ አካታች የሆኑ የምክክር መድረኮችን በማመቻቸት ለዘላቂ ሰላም እና ለጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚረዱ ምክረ ሀሳቦችን የማቅረብ ግብም አለው። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥ በየክልሎቹና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተወካዮች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎችን በስፋት አከናውኗል። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ብልፅግና ፓርቲ ምክክር ኢትዮጵያን ጠንካራ ሀገር ያደርጋታል የሚል ፅኑ እምነት እንዳለው ገልፀዋል። ብልፅግና ፓርቲ በሀገራዊ ምክክር የእስካሁን ሂደት ውስጥ ግልፅ የሆነ አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መቆየቱንም አስታውሰዋል። የምክክር ሂደት ለዘመናት የተሻገረና ከሀገረ መንግስት ግንባታ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በዘመናት መካከል በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው ያሉት አቶ መለሰ፤ ፓርቲው ምክክርን የአንድ ወገን ሥራ አድርጎ እንደማይመለከተውም ተናግረዋል። ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ መሆኑን በማመን፣ ፓርቲው በውይይት በመሳተፍና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ይበጃሉ ያላቸውን አጀንዳዎች በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እንደ ገዥ ፓርቲም ሂደቱ እንዲሳካ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን አክለዋል። የምክክር ሂደቱ ለስምንት ወራት መራዘሙ ኮሚሽኑ ሥራውን በአግባቡና በጥራት እንዲያጠናቅቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ብልፅግና ፓርቲም በቀጣይ ወራት ለሀገራዊ መግባባት እየተካሄደ ላለው ምክክር አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በዚህም ፓርቲው ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ የመግባባት ደረጃ ላይ እንድትደርስ ይሰራል ብለዋል። ብልፅግና ፓርቲ የምክክር ሂደት ለትውልድ የሚኖረውን የላቀ ፋይዳ በሚገባ የሚገነዘብ በመሆኑ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሁሌም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በትግሪኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ካስተላለፏቸው መልዕክቶች
Mar 3, 2026 155
ለትግራይ ሕዝብና ወጣቶች ያስተላለፉት መልዕክት፡- "የትግራይ ሕዝብ ከጦርነት ይልቅ ሰላምና ልማት ይገባዋል" ብለዋል። ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ መክረዋል። መንግሥት በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት ጽኑ ፍላጎት እንዳለውና ለዚህም ማንኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል አረጋግጠዋል። የሰሜኑን ጦርነት መንስኤዎች በተመለከተ ህወሓት ከ50 ዓመት በፊት በነበረ ኋላቀር አስተሳሰብ የታሰረ መሆኑና ለውጥን ለመቀበል አለመፈለጉ። ዓለም በቴክኖሎጂና በ"ፕራግማቲዝም" በምትመራበት ዘመን፣ ድርጅቱ በአሮጌው መንገድ ለመጓዝ መሞከሩ ለግጭት ዳርጎታል። ቆሞ ቀሩ ኃይል "ኢትዮጵያ ትፈርሳለች" የሚል የተሳሳተ ስጋት በመዝራት የለውጡን ኃይል እንደ ጠላት ማየቱ። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊነት በተመለከተ ፡- መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ሰላም እንዲያገኝ ባንክ፣ መብራትና ቴሌኮም የመሳሰሉ አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲመለሱ ማድረጉን ገልጸዋል። ሆኖም ቆሞ ቀሩ ቡድን ስምምነቱን "መርጦ የመተግበር" ዝንባሌ እያሳየ መሆኑን ተችተዋል። በተለይም ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ውሳኔ አለማክበሩን ጠቅሰዋል። ድርጅቱ ለልማት የተመደበውን በጀት ለጦርነት ዝግጅትና ለታጣቂዎች ቀለብ እየዋለ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም በትግራይ ሕዝብ ላይ ተጨማሪ መከራ እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በጦርነቱ ወቅት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ፡- ጦርነት ሁልጊዜም አስከፊ ገጽታ እንዳለው ገልጸው፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሽግግር ፍትሕ (Transitional Justice) አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ ሂደት ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ በሆነ መንገድ ሊካሄድ እንደሚገባውና ወንጀል የፈጸሙ አካላት በሕግ መጠየቅ እንዳለባቸው ገልጸዋል። የኤርትራ መንግሥት (ሻዕቢያ) ሚና በጦርነቱ ወቅት የኤርትራ ጦር ያደረገው ድጋፍ የሚታወስ መሆኑን ጠቅሰዋል። ሆኖም በጦርነቱ ሂደት የተፈጸሙ ማናቸውም ዓይነት ጥፋቶች፣ ግድያዎችና ዘረፋዎች (በተለይም በአክሱም፣ ዓድዋና ሽሬ አካባቢዎች) የማይቀበሉትና የሚወገዝ ተግባር መሆኑን በግልጽ አስታውቀዋል። መንግሥት ማንኛውንም የውጭ ኃይል ጣልቃ ገብነት እንደሚቃወምና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር እንደሚሠራ ገልጸዋል።
የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤን የማስቀጠል አባዜ ምክንያት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Mar 3, 2026 125
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው የህወሓት አመራር ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤ የማስቀጠል አባዜ ምክንያት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ቆይታ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የሰሜኑ ጦርነት መነሻ ምክንያቶችን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፤ ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና እኔ ብቻ በሚል ስሜት በመዋጡ ግጭት እንዲነሳ መንስኤ መሆኑን ገልጸዋል። ህወሓት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብ የታሠረ ድርጅት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ብቻ ሳይሆን ዓይኑን ጨፍኖ ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ ርምጃዎችን ሲወስድ መቆየቱንም ተናግረዋል። የለውጡ ኃይል የጀመረውን ጉዞ ለማደናቀፍ መሞከሩን ገልጸው፤ በህወሓት ቆሞ ቀር አስተሳሰብ የተነሳው ጦርነት ጉዳት ማስከተሉንም አንስተዋል። ሁለተኛው ቁልፍ ምክንያት ደግሞ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ ጋር የተሣሠረ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ህወሓት ኢትዮጵያ በጥርጣሬና በሥጋት ውስጥ እንድትኖር መስራቱ ለችግሮች መባባስ ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል። ቆሞ ቀሩ ኃይል ከ50 ዓመት በፊት ከነበረው አስተሳሰብ ውጭ ሊንቀሳቀስ አለመቻሉን ጠቅሰው፤ ይህ ደግሞ ከለውጡ ጋር አብሮ ለመሄድ እንዳላስቻለው ገልጸዋል። የለውጥ ኃይሉ ዓለምን ያስደመመ ተአምራዊ ለውጦችን ማምጣቱን ጠቅሰው፤ ቆሞ ቀር ኃይሉ ከለውጥ ኃይሉ ጋር ተስማምቶ ሕዝቡንና ነፍሱን እንደመለወጥ የልማት ሽታ ከማያውቁ ኋላቀሮች ጋር እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ ያለው የፖለቲካ ስብራት ሌላኛው መንስኤ እንደሆነ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተሳሳተ ትርክት ላይ የተመሰረተው ፖለቲካዊ መዋቅር የፖለቲካ ስርዓቱ እንዲበላሽ ማድረጉን ነው ያብራሩት። ጦርነቱ የራሱ ልዩ ገጽታዎች እንዳሉት ሆኖ ከሀገራዊ መዋቅር ችግር የተለየ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባውም ብለዋል። ይህ አዙሪት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መሰበር አለበት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይሄንን ለመስበር ደግሞ ኃላፊነት መውሰድ እንደሚገባ ገልጸዋል። እንደ ትውልድ ይበቃል ብለን መሥራት አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የመንግስት አቋም ችግሮችን በውይይት መፍታት አማራጭ የሌለው መንገድ እንደሆነ በጽኑ እንደሚያምንም ገልጸዋል። ይሄንን ለማድረግ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ወሳኝ ሀገራዊ መፍትሔ ሊሆን ይችላል ብለን እናምናለን ብለዋል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ እስካሁን ከሞላ ጎደል ከትግራይ ውጭ አብዛኛው ሥራ እየተገባደደ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በትግራይ ክልል ግን ውይይት እንዳይደረግ፣ ሕዝባችን ቁጭ ብሎ እንዳይወያይ፣ ጥያቄ አንሥቶ መፍትሔ እንዳያገኝ፣ ያ ቆሞ ቀር ኃይል ሆን ብሎ እየሠራ ይገኛል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ደግሞ ትክክለኛ አካሄድ ነው ብዬ አላምንም ብለዋል።
ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል
Mar 3, 2026 139
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት መቻሉን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። ዛሬ "የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግሥት ግንባታ!" በሚል መሪ ሀሳብ በዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት ቅንጅት ላይ የሚያተኩር ሀገራዊ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት የፍርድ ቤቶች የለውጥ ተግባራትን አስመልክቶ ባቀረቡት የመነሻ ሐሳብ፤ የዳኝነት ነጻነትን ለማጠናከር የሕግ ማሻሻያ መደረጉን ተናግረዋል። ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አኳያም ግልጽ ችሎትን የማስፋፋት ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፤ ግልጽ ችሎት ከነበረበት 65 በመቶ ወደ 91 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። ፍርድ ቤቶች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ድምፅን ወደ ጽሁፍ የሚቀይር ቴክኖሎጂን በመጠቀም ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ኮሚሽኑ እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እስካሁን ውጤታማ የሚባሉ ሥራዎችን ሰርቷል ብለዋል። የሀገሪቱን ሁሉንም ክልሎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ 93 በመቶ ማካተት መቻሉን ጠቁመው፤ በቀጣይም አጀንዳ መቅረጽና ይፋ ማድረግ እንዲሁም ሀገራዊ ምክክር ማካሄድ ከሚከናወኑ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ የቦርዱን የለውጥ እና ቀጣይ ተግባራት ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ቦርዱ ባለፉት ዓመታት ተቋማዊ የሕግ ማሻሻያዎችን በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዕጩዎችን ምዝገባ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል በማከናወን ማጠናቀቅ መቻሉን ተናግረው፤ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስልጠና መሰጠት መቻሉንም ገልጸዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬታማነት ለማከናወን "ምርጫዬ" የመራጮች መመዝገቢያ የዲጂታል አማራጭ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ፤ ነጻና ገለልተኛ ተቋም ለመገንባት የአዋጅ ማሻሻያ፣ ደንብና መመሪያዎችን ማሻሻል መቻሉን ገልጸዋል። ከኦዲት ሽፋን አኳያም የፋይናንሻል ኦዲት መቶ በመቶ ማከናወን መቻሉን በመጥቀስ፤ የክዋኔ ኦዲትንም ከ24 ወደ 41 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል። የኢትየጵያ ሕዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ከለውጡ ወዲህ በተከናወኑ የለውጥ ስራዎችም ከአሰራርና ከሰው ሃይል አኳያ፣ የሕግ ማሻሻያ ተግባራት፣ ከቴክኖሎጂ አኳያ እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራሮች ተዘርግተው ስኬታማ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ከቴክኖሎጂ ስራዎች ለግልጸኝነት፣ ለተጠያቂነት፣ ለቅልጥፍና እንዲሁም ለውጤታማነት ምቹ መደላድል መፍጠራቸውን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ፤ ከለውጡ በፊት ኮሚሽኑ ገለልተኛ እና ውጤታማ ያልነበረ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ምቹ የሕግ ማዕቀፍ፣ አዲስ የሰው ሃብት መዋቅር፣ ብቃትና አቅም ያለው አመራር መፍጠር፣ ሥራን የሚያቀላጥፉ በቴክኖሎጂ የተደገፉ መፍትሔዎች፣ የመረጃ ስርዓት በቴክኖሎጂ የሚመራ መደረጉ እንዲሁም የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ መቻሉን ጠቁመዋል። የመድረኩ ታሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉን አድንቀዋል፡፡ ይህም ለሀገረ መንግስት ግንባታ ብሎም ለዘላቂ ልማትና ለሕዝቦች ተጠቃሚነት መረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በሰጡት ማጠቃለያ፤ ለምክር ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት በሕግ የተሰጣቸውን ሥልጣንና ኃላፊነት በገለልተኝነትና በነፃነት እየተወጡ ይገኛሉ። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዳኝነትና ዲሞክራሲ ተቋማት ላይ መሠረታዊ የሪፎርም ሥራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። ተቋማቱ ላይ ከተከናወኑ የለውጡ ስራዎች መካከል የማቋቋሚያ አዋጆቻቸውን በድጋሚ መፈተሽና ማሻሻል፣ የአመራር ሥርዓታቸውን ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ፣ ዘመናዊና ግልጽነት ያለው የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት መቻል ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል፡፡ የተቋማት ግንባታ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ነው ያሉት አፈ-ጉባኤው፤ ተቋማቱ ነፃ ሆነው እንዲሠሩ መደረጉ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ዴሞክራሲን እውን ለማድረግ ትልቅ መሠረት እንደሚጥል አጽንኦት ሰጥተዋል። ተቋማቱ በገለልተኝነት መሥራታቸው ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን ለማፋጠን ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ጠቁመዋል።
ማህበራዊ
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የዳበረ አብሮነት የከተማዋን ምሳሌትነት እያደመቀ ነው
Mar 4, 2026 66
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በመተሳሰብ የዳበረ አብሮነት የከተማዋን ምሳሌትነት እያደመቀ እንደሚገኝ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የእስልምና እምነት ተከታዮች የኢፍጣር መርሐ-ግብር አክሂዷል። የአሥተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደ ከተማ አሥተዳደር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች በማስታወስ በጋራ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ማዘጋጀቱ ትልቅ ደስታ እንደሚሰጥ ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የእምነት ልዩነት ያልገደበው ተሳስቦና ተረዳድቶ በአንድነት የመኖር ጥበብ የከተማዋን ተምሳሌትነት እያደመቀ እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የኢፍጣር ሥነ-ሥርዓቱም የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር ያለውን ጠንካራ ትስስር በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም መሰል የመደጋገፍና መረዳዳት ዕሴቶች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል። በኢፍጣር መርሐ-ግብሩ ላይ የተሳተፉት የእምነቱ ተከታዮችም በከተማ አሥተዳደሩ ለተደረገላቸው ዝግጅት ምሥጋና አቅርበዋል።
የአፈጣጠር ችግር ያለባቸው ህጻናት ምቹና ተደራሽ የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Mar 4, 2026 82
ጎንደር፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ) ፡-በኢትዮጵያ የአፈጣጠር ችግር ያለባቸው ህጻናት ምቹና ተደራሽ የጤና አገልግሎት የሚያገኙበትን የህክምና ስርአት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የጎንደር ዩንቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአፈጣጠር ችግር ላለባቸው ህጻናት ያቋቋመው የኒውሮሰርጀሪና የፊዚዮቴራፒ ህክምና አገልግሎት መስጫና ማገገሚያ ማእከል ተመርቆ ተከፍቷል፡፡ በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ በሚኒስቴሩ የስፔሻሊቲና ተሃድሶ ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ኤርሚያስ ሙላቱ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ የአፈጣጠር ችግር ያለባቸው ህጸናት በቂ የህክምና አገልግሎት የሚያገኙበት አንድ ወጥ ስርአት ባለመዘርጋቱ ህጸናቱን ተደራሽ የሚያደርግ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ውስንነቶች አሉ። አገልግሎቱን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ እንዲቻል የህክምና ባለሙያዎችን አቅም ከማጎልበት ጀምሮ ለህክምና አሰጣጡ አጋዥ የሆኑ መድሃኒቶችንና የህክምና መሳሪያዎችን በማሟላት ረገድ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በህጻናት የአፈጣጠር ችግር ከሚስተዋሉ የጤና እክሎች መካከልም የከንፈርና የላንቃ መሰንጠቅ፣ የነርቭ ዘንግ ክፍተት፣ የአጥንትና ጡንቻ መላላትና የአእምሮ እድገት ውስንነት ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ያቋቋመው ማእከል የአፈጣጠር ችግር ያለባቸው ህጻናት የተሟላ ህክምና አግኘተው ጤናማና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ የሚያግዝ እንደሆነም አመልክተዋል፡፡ በምክትል ፕሬዝዳንት ማእረግ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ጌታው ብርሃን የማእከሉ መቋቋም የአፈጣጠር ችግር ያለባቸው ህጻናት አገልግሎቱን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። ማእከሉ አገልግሎቱን በጥራት ለመስጠት መዘጋጀቱንም ተናግረዋል፡፡ ማእከሉ የአፈጣጠር ችግር ላለባቸው ህጻናት የቀዶ ህክምናን ጨምሮ በረጅም ጊዜ ሂደት አገግመው ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ በማድረግ በኩል አካላዊና ስነ ልቦናዊ ድጋፎችን እንደሚያደርግ የገለጹት ደግሞ የማእከሉ አስተባባሪ ረዳት ፕሮፌሰር ኢሳያስ አደፍርስ ናቸው፡፡ ሪች አናዘር ፋውንዴሽን የተባለ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅትም ግምታቸው ከአራት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የአካል ድጋፍ ቁሳቁሶችንና ዘመናዊ የአልትራሳውንድ የህክምና መሳሪያዎችን ለማእከሉ መለገሱንም ተናግረዋል፡፡ የአፈጣጠር ችግር የህክምና አገልግሎት ሳምንት ንቅናቄ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተካሄደ መሆኑ ተመልክቷል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል
Mar 4, 2026 91
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ገለጹ። በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8) አስመልክቶ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ የሴቶችን እኩልነትና መብቶች ለማስከበር በርካታ መስዋዕትነት ያስከፈሉ ትግሎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ የዚህ ትግል ውጤትም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እውቅና በማግኘት የሴቶችን መብት የሚያስከብሩ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎች እንዲወጡ ፋና ወጊ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ በሰጠው ልዩ ትኩረት በኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ተጨባጭ ለውጦች መታየታቸውን ጠቁመዋል። በፖለቲካዊ ውሳኔ ሰጪነት ረገድ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች ውክልና 41 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው በሚኒስትሮች ምክር ቤት የሴቶች ተሳትፎ 50 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል፡፡ የዘንድሮው የሴቶች ቀን አከባበር ባለፉት 50 ዓመታት የተከናወኑ ስራዎችንና የተገኙ ውጤቶችን ከመገምገም ባለፈ በቀጣይ የሚቀሩ የቤት ስራዎች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡ በዓሉን በማስመልከት ህብረተሰቡን ያሳተፉ ሰፋፊ ንቅናቄዎች የሚከናወኑ ሲሆን ኤግዚቢሽንና ባዛሮች፣ የጡት ካንሰር ምርመራ፣ የማህፀን በር ካንሰር ምርመራና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እንደሚከናወኑም ጠቁመዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “50ኛው ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል።
ሪፎርሙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሀገረ መንግስት ግንባታ ላይ የሚኖራቸውን ሚና አጎልብቷል
Mar 4, 2026 153
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሪፎርም በኢትዮጵያ የሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ላይ የድርጅቶቹን ሚና ማጎልበቱን የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ ገለጹ። አምስተኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ከየካቲት 26 ቀን 2018 ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እንደሚካሄድ የባለሥልጣኑ መሥሪያ ቤት አስታውቋል። የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ ለኢዜአ እንደገለፁት፣ ድርጅቶቹ በሀገረ መንግሥት ግንባታና በልማት እንቅስቃሴዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ድርጅቶቹ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች ላይ የሚያደርጉት ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ይህ ውጤት ሊገኝ የቻለው በሪፎርሙ አማካኝነት ለሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እንቅስቃሴ ምቹ መደላድል በመፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በኢትዮጵያ የሀገረ መንግስት ግንባታ ላይ ሚናቸው የጎላ ነው የሚል አስተሳሰብ ጎልብቷል ነው ያሉት። በአምስተኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ድርጅቶቹ ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ እድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ በማስተዋወቅ ረገድ የሚኖረውን ፋይዳ ታሳቢ በማድረግ ከነገ የካቲት 26 እስከ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል ብለዋል። በሁነቱ ላይ ከዘርፉ ጋር በተያያዙ አጀንዳዎች ዙሪያ የፓናል ውይይት የሚካሄድ ሲሆን፣ 123 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት ኤግዚቢሽን እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። እነዚህ የፓናል ውይይቶች የሀገርንና የሕዝብን ጥቅም በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ በመምከር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ጠቃሚ ሐሳቦችን ለማመንጨት ያስችላሉ ብለዋል። አክለውም የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ከመንግስት፣ ከግሉ ዘርፍና ከልማት አጋሮች ጋር ያላቸውን ትስስር በማጠናከር ለሀገር እድገት በተሻለ ሁኔታ እንዲሰሩ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ህብረተሰቡ፣ ተቋማትና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በአምስተኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ላይ በመገኘት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።
ኢኮኖሚ
ሀዋሳ ከተማን ምቹ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው - ከንቲባ ጥራቱ በየነ
Mar 4, 2026 85
ሀዋሳ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለፁ። የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 24ኛ መደበኝ ጉባኤውን አካሂዷል። የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ስድስት ወራት ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ ከተማዋን በማዘመን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ ናቸው። በተለይ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በከተሞች የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ በሃዋሳም ተግባራዊ መደረጉ ከተማዋን ምቹ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። በከተማዋ አመራሩን፣ ህብረተሰቡንና ባለሙያዎችን በማቀናጀት እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ውጤት የተመዘገበበት መሆኑንም ከንቲባው ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም 8 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በሚሸፍን ሁለተኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ አዲስ የተሽከርካሪ፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችን ጨምሮ የአረንጓዴ ስፍራዎች ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። የኮሪደር ልማቱ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ የሕፃናት መጫዎቻዎች፣ መፀዳጃ ቤቶች፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ የታክሲ መጫኛና ማውረጃን ጨምሮ ተርሚናሎች እንዳሉትም አስረድተዋል። ሕብረተሰቡ ለኮሪደር ልማቱ ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ358 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ የሚተመን ድጋፍ አድርጓል ብለዋል። እንደከቲባው ገለጻ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ከማስዋብ በተጨማሪ ለበርካታ ወጣቶችም ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል ለመፍጠር አስችሏል። በአረንጓዴ ልማትና በፅዳት ሥራም ህብረተሰቡን በማሳተፍ ፅዳትና ውበትን በዘላቂነት ለመጠበቅ የተደረገው ጥረትም አመርቂ ውጤት ተገኝቶበታል ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ ገቢን በማሳደግ፣ የሥራ ባህልን በመቀየር፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ባከናወናቸው ተግባራት እመርታ እንደታየም አመልክተዋል። የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ደምሴ ዳንጊሶ በበኩላቸው፤ በኮሪደር ልማት ሥራዎች የታየው አፈፃፀም የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ፍሰቱን ለማሳደግ አስችሏል ነው ያሉት። ምክር ቤቱ በከተማዋ የተጀመሩ የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎች ዘላቂ እንዲሆኑ የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ከምክር ቤት አባላት መካከል አቶ ዘላለም ላሌ፤ በከተማዋ በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ለኢኮኖሚ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። ከሥራ ዕድል ፈጠራና ከሥራ ባህል መጎልበት አኳያም እየታየ ያለው ለውጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ነው የገለጹት። መልካም አስተዳደርን ለማስፋነና ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴን ከመከላከል አንፃር የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ፍትሃዊ የመሰረተ-ልማት ስርጭትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል
Mar 4, 2026 86
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት ፍትሃዊ የመሰረተ-ልማት ስርጭትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስኬታማ ተግባራት ማከናወኑን የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለፁ። የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮችና የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ጋር በመተባበር የሚያካሂደውን የኢትዮጵያ የመሠረተ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንት አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንት ለመጀመሪያ ጊዜ "ኢትዮጵያ ትገነባለች ፈጠራ፣ ፍጥነት እና ጥራት ለመሰረተ ልማት እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ከሚያዝያ 9 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እንደሚካሄድ ተገልጿል። በዚህ ወቅት የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንዳሉት የመሰረተ-ልማትና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዘርፉ ከግብርና ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ኃይል የሚያሳትፍና ሰፊ የስራ እድሎችን በመፍጠር ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ማደግ ጉልህ ድርሻ ያለው መሆኑን ገልፀዋል። መንግስት ፍትሃዊ የመሰረተ-ልማት ስርጭትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስኬታማ ተግባራት ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል። በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ የኃይል ማመንጫና የመስኖ ግድቦች እንዲሁም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሀገሪቱ ለዘርፉ የሰጠችውን ትኩረት የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንት ሀገሪቱ በመሰረተ-ልማት ዝርጋታ ያሳካችውን ስኬቶችና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የተሰሩ ስራዎችና ቀጣይ ትልሞች የሚቀርብበት መድረክ እንደሚሆን ተናግረዋል። ለአራት ቀናት በሚካሄደው መርሃግብር የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ተዋናዮች፣ የፈጠራ ባለቤቶችና የግንባታ ግብዓት አቅራቢዎች ይሳተፋሉ ብለዋል። መርሃግብሩ የግንባታ እቃዎችና ማሽነሪዎች እንዲሁም ዲጂታል የግንባታ ቴክኖሎጂዎች የሚቀርቡበት መሆኑን ጠቁመዋል። የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ለጠቅላላ ሀገራዊ ምርት እስከ 20 በመቶ ድርሻ እንዳለው ገልፀው፤ በኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት እድገትና የብልፅግና ጉዞ መሰረት ሆኖ እንዲቀጥል የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ሀገሪቱ ባላት የተፈጥሮ ሀብት በመጠቀም ከውጭ የሚገቡ የኮንስትራክሽን ግብዓቶችን ተኪ ምርት ምርታማነትን የሚያበረታታ ነው ብለዋል። የተሻለ አፈፃፀምና አደረጃጀት ያላቸው ተቋራጮችና አማካሪዎች እውቅና የሚሰጥበትና በኮንስትራክሽን ዘርፉ አዳዲስ አሰራሮችና የግንባታ ዘዴዎች እንዲተዋወቁ የሚያደርግ እንደሚሆንም ገልፀዋል።
ሚኒስቴሩ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቁ የሰው ኃይል ለማቅረብ ይሰራል
Mar 4, 2026 101
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛና በሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቁ የሰው ሃይል ለማቅረብ እንደሚሰራ ተገለጸ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጋር በሰው ሃይል አቅርቦት እና ስልጠና ዘርፎች በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የሰው ሀብት አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ በቀለ ባይ ተፈራርመውታል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት ስምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በሰው ሃይል አቅርቦት፣ ስልጠና ዘርፎች በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸው ነው። ሚኒስቴሩ በስሩ ባሉ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ፣ በሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት እንዲሁም ሌሎች ተጠሪ ተቋማት በኩል ለአየር መንገዱ ብቁ የሰው ሃይል ለማቅረብ እንደሚሰራ ጠቁመዋል። ለዚህም ስምምነቱን ወደ ስራ ለማስገባት ዝርዝር ዕቅዶች ተዘጋጅቶ የሁለቱ ተቋማት የስትሪንግና ቴክኒክ ኮሚቴ በጋራ ርብርብ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ ይበልጥ ተወዳዳሪ እንዲሆን በማድረግ በኩል ስምምነቱ አወንታዊ ሚና እንደሚኖረውም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የሰው ሀብት አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ በቀለ ባይ በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ በየአመቱ በአማካይ ከ3500 እስከ 4000 ሰዎችን በቅጥር እንደሚቀበል ተናግረዋል። አየር መንገዱ ከስራና ክህሎት ጋር በጋራ መስራቱ የቅጥር ሂደቱን ውጤታማ ከማድረግ ባለፈ የስራ ድግግሞሽን የሚያስቀር ትልቅ እርምጃ ነው ብለዋል።
በባህርዳር ከተማ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል
Mar 4, 2026 69
ባህርዳር፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፡-በባህርዳር ከተማ ሰላምን በማፅናት የተጀመሩ ውጤታማ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ገለፁ። የባህርዳር ከተማ አስተዳደር "ለሰላም ዘብ ዕንቆማለን፤ የልማት አርበኛ እንሆናለን" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል። ምክትል ከንቲባው አቶ አስሜ ብርሌ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ አመራሩ፣ የፀጥታ ኃይሉና ሕዝቡ በቅንጅት ያከናወኑዋቸው ተግባራት ውጤታማ ናቸው። በኮሪደር ልማት፣ በመንገድ፣ በስማርት ሲቲ ግንባታ፣ በመሶብ አንድ ማዕከል የአገልግሎት መስጫና ዲጂታላይዜሽን ትግበራ ላይ የተከናወኑት ተግባራት ከተማዋን ከማዘመን ባለፈ ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ አስችለዋል ነው ያሉት። እየተከናወኑ የሚገኙ የሰላም፣ የልማትና ለመልካም አስተዳደር ተግባራትን ቀጣይነት እንዲኖራቸው ለማድረግም ከማሕበረሰቡ ጋር በቅንጅት የሚከናወኑ ስራዎች ትኩረት እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል። በተለይም በመጭው ግንቦት ወር 2018 ዓ.ም የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን አጠናክሮ መሔድ ያስፈልጋል ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ የህዝብ ግንኙነት አማካሪ አቶ ሞላ ሁሴን በበኩላቸው፤ አመራሩ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በቅንጅት በመስራቱ የከተማው ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ እንዲገኝ ማድረጉን አስረድተዋል። ይህም የከተማዋን ገፅታ በመሰረታዊነት ከመቀየር ባሻገር ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሁሉን አቀፍ የልማት ተግባራት ለማከናወን ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም ነው ያመለከቱት። ''ከግጭት የሚገኝ ትርፍ እንደሌለ መረዳት ይገባል'' ያሉት የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ዘውዱ ዘለቀ በተለይም ወጣቱ ወደ ሰላም በመምጣት ተግቶ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል። በከተማዋ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት የከተማዋ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን ገልፀዋል። በንቅናቄ መድረኩም የአስተዳደሩ፣ የክፍለ ከተማና የቀበሌ አመራሮች ተሳትፈዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በክልሉ ኮሌጆች ከስልጠና በተጨማሪ ለቴክኖሎጂና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል
Mar 4, 2026 72
ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለቴክኖሎጂና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው ተገለጸ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የሶዶ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥራ እንቅስቃሴን ዛሬ ተመልክተዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ የሚገኙ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች እንዲሁም ቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከስልጠና ሥራቸው በተጨማሪ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በሥራ ዕድል ፈጠራ ዜጎችን ተጠቃሚ ሊያደርጉ ይገባል፡፡ በተለይ በኮሌጆቹ የሚሰጡ ስልጠናዎች የህዝብን ችግር የሚፈቱ ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያስችሉ መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ከማፍራት ባለፈ ስልጠናውን ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር በማቀናጀት የዜጎችን በተለይ የወጣቱን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በዚህም ተቋማቱ የውስጥ ገቢያቸውን በማጎልበት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ እንዳለባቸው ተናግረዋል። ኮሌጆቹ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ማፍራት እንዳለባቸው ያሳሰቡት አበባየሁ (ዶ/ር)፣ ውጤታማ የስልጠናና የፈጠራ ሥራዎችን እንዲያከናውኑም የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል ያጠናክራል ብለዋል። የዛሬው የመስክ ምልከታም በዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን ለይቶ ለመፍታትና ጠንካራ ጎኖችን ለማስቀጠል ያለመ መሆኑን ነው የገለጹት። የሶዶ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ኢንጂነር ያዕቆብ ያሲን በበኩላቸው ኮሌጁ በአውቶሞቲቭ፣ በሆቴልና ቱሪዝም፣ በአግሮ ፕሮሰሲንግ እንዲሁም በሌሎች የሙያ መስኮች ብቁ ዜጎችን ለማፍራት እየሰራ ይገኛል። ኮሌጁን የዲጂታል ማዕከል ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፣ ለዚህም በአሁኑ ወቅት ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የዳታ ማዕከል ተገንብቶ ለአገልግሎት በቅቷል ብለዋል። ኮሌጁ በአሁኑ ወቅት 1ሺህ 944 ሰልጣኞችን ተቀብሎ እያሰለጠነ ሲሆን የስልጠና ሂደቱም ከሀገር ውስጥ ባለፈ በውጭ አገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለመሆን እያገዘ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስክ ምልከታው ላይ የክልሉ፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዜጎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል
Mar 4, 2026 96
ሰመራ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዜጎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚያስችል የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ዓሊ ተናገሩ። ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የዲጂታል ጉዞ ቀጣይ 5 ዓመታት የሚመራበትን ''ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ'' በቅርቡ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ በሁለንተናዊ ዘርፍ በተለይም የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ አጋዥ ሚና ይኖረዋል። በዚህ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ዓሊ እንዳሉት ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ስርዓቱን ለማዘመን እያገዘ ነው። ዘመኑ ያፈራውን የዲጂታል አሰራር እውን በማድረግ በቀላሉ መግባባት፣ መረጃዎችን መቀባበልና በተለይም የግብይትም ሆነ ሌሎች አገልግሎቶችን በፍጥነት ለማግኝት እንደሚረዳ ነው የገለጹት። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማፋጠንና ከዘርፉም ቀጣይነት ባለው መልኩ ተጠቃሚ መሆን ያስችላል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት የስማርት ሲቲ ግንባታን ጨምሮ በየደረጃው ዲጂታል አሰራር በመተግበር እየታዩ ያሉ ለውጦች የሚያበረታቱ በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ሲሉም ገልጸዋል። ስትራቴጂው መረጃዎችን በቀላሉ የመመዝገብ፣ የማስቀመጥና የመለዋወጥ ስራን ቀላልና ፈጣን ማድረጉንም ለአብነት አንስተዋል። በዋናነት የመንግስት አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ጥራት ያላቸው በማድረግ በኩል ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ 30 ሚሊዮን የገጠር መሬት ማሳዎች በዲጂታል የመረጃ ሥርዓት ተመዝግበዋል
Mar 3, 2026 92
ቦንጋ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፡- በሀገር አቀፍ ደረጃ 30 ሚሊዮን የገጠር መሬት ማሳዎች በዲጂታል የመረጃ ሥርዓት መመዝገባቸውን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የግብርና አገልግሎቶችን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ተግባር እየተከናወነ ነው የግብርና ሚኒስቴር ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጋር በመተባበር ''ዲጂታል ማንነት ለተረጋገጠ ይዞታ ባለቤትነትና ለላቀ የፋይናንስ ተጠቃሚነት'' በሚል መሪ ሀሳብ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። በግብርና ሚኒስቴር የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈፃሚ ትዕግስቱ ገብረ-መሥቀል እንደገለጹት፣ ሀገራዊ የገጠር መሬት አስተዳደር ሥርዓቱን ለማዘመን በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉ 50 ሚሊዮን ማሳዎች ውስጥ እስካሁን ድረስ 30 ሚሊዮን የሚሆኑት በዲጂታል መረጃ ሥርዓት ተመዝግበው አርሶ አደሩ የይዞታ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት እንዲያገኝ ተደርጓል ብለዋል። የመረጃ ማዘመን ስራው በአሁኑ ወቅት በ516 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ መደረጉንም ነው ያመለከቱት። አርሶ አደሩ መሬቱን በዋስትና በማስያዝ እስካሁን 10 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የብድር አገልግሎት ማግኘት መቻሉንም አብራርተዋል። በተያዝነው በጀት ዓመት 12 ሚሊዮን አርሶ አደሮችን የፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፣ የመረጃ ስርዓቱን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር አካታች የፋይናንስ ስርዓት ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የዲጂታል መታወቂያ ከይዞታ ማረጋገጫ ጋር መገናኘቱ አርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ይበልጥ ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ በክልሉ የታቀደውን ግብ ለማሳካት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሀብታሙ ካፍትን እና የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፣ የዲጂታል አሰራሩ ለዓመታት ሲነሳ የነበረውን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር እንደሚቀርፍ ጠቁመዋል። መረጃን በዘመናዊ መልኩ ማደራጀትና አርሶ አደሩን የፋይዳ መታወቂያ ባለቤት ማድረግ ላይ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። በመድረኩም የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የስራ ሃላፊዎች፣ የኢትዮ ቴሌኮምና የኢትዮ ፖስታ አገልግሎት የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የግብርና አገልግሎቶችን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ተግባር እየተከናወነ ነው
Mar 3, 2026 103
ቦንጋ፣ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የግብርና አገልግሎቶችን የማዘመንና ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ተግባር እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ። በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት ይገባል የክልሉ ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር “ዲጂታል ማንነት ለተረጋገጠ ይዞታ ባለቤትነትና ለላቀ የፋይናንስ ተጠቃሚነት!'' በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የንቅናቄ መድረኩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለፁት፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ የፋይዳ መታወቂያን ማዳረስ አንዱ ነው። በአሁኑ ወቅትም የገጠር ትራንፎርሜሽንን እውን ለማድረግ ፈጣንና ዘመናዊ የግብርና አገልግሎቶችን ለአርሶና አርብቶ አደሩ መስጠት እንዲቻል እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።ለዚህም የፋይዳ መታወቂያን የማዳረስ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የግብርና አገልግሎቶችን በማዘመን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር የአርሶና አርብቶ አደሩን የብድርና የፋይናንስ ተጠቃሚነት ችግር ለመፍታት እንደሚያስችልም ነው የገለጹት። ይህም አርሶና አርብቶ አደሩ ባለው እሴት ላይ ተመርኩዞ የፋይናንስ ተጠቃሚ እንዲሆን እንደሚያግዘው ነው የተናገሩት። የአርሶና አርብቶ አደሩ ዋነኛ ሀብት የሆነውን የመሬት ልኬትን ከሀገራዊ መረጃ ስርዓት ጋር በማቆራኘትና ከዲጂታል መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር የፋይናንስ ተደራሽነትን የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል። በክልሉ በከተማና በገጠር ከ682 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ መቻሉንም ገልጸዋል።
ስፖርት
የሊጉ መሪ አርሰናል ድል ሲቀናው ማንችስተር ሲቲ ነጥብ ጥሏል
Mar 4, 2026 55
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ29ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ ማምሻውን በመካሄድ ላይ ናቸው። በአሜክስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አርሰናል ቡካዮ ሳካ በዘጠነኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ጎል ብራይተንን 1 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል ነጥቡን ወደ 67 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ማንችስተር ሲቲ እና ኖቲንግሃም ፎረስት ሁለት አቻ ተለያይተዋል። በኢትሃድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አንቶዋን ሴሜንዮ እና ሮድሪ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሞርጋን ጊብስ-ዋይት እና ኤልዮት አንደርሰን ለፎረስት ጎሎቹን አሳርፈዋል። ማንችስተር ሲቲ በ60 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀራቸው ውሃ ሰማያዊዎቹ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያላቸው የነጥብ ልዩነት በነበረበት ወደ ሰባት ከፍ ብሏል። ሲቲ በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ነጥብ ጥሏል። ቼልሲ አስቶንቪላን ከሜዳው ውጪ 4 ለ 1 አሸንፏል። ጆአኦ ፔድሮ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል።ኮል ፓልመር ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ዳግላስ ሉዊስ ለአስቶንቪላ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ በ48 ነጥብ አምስተኛ፣ አስቶንቪላ በ51 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዘዋል። በሌላኛው ጨዋታ ዌስትሃም ዩናይትድ በክሪሴንሲዮ ሳመርቪል ጎል ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል መንገድ ተመልሷል
Mar 4, 2026 59
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ21ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ አርባምንጭ ከተማን 4 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ሀብታሙ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር አንዋር በድሩ እና ሩዋንዳዊው ፓትሪክ ሲቦማና ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ይገዙ ቦጋለ የአርባምንጭ ከተማን ብቸኛ ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከስድስት የሊግ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ31 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርባምንጭ ከተማ በ16 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ወላይታ ድቻ እና ሃዋሳ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቴዎድሮስ ታፈሰ ለወላይታ ድቻ፣ ብሩክ ታደለ ለሃዋሳ ከተማ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ወላይታ ድቻ በ23 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሃዋሳ ከተማ በ37 ነጥብ ደረጃውን ከሶስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። ቡድኑ ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሶስት የማጥበብ እድል አልተጠቀመበትም። ዛሬ ቀን ላይ በተደረጉ የ22ኛ ሳምንት ጨዋታዎች የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ኢትዮጵያ ቡና ባህርዳር ከተማን 2 ለ 0 ረቷል።
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ ውድድርን ልታዘጋጅ ነው
Mar 4, 2026 97
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም አትሌቲክስ ውድድርን ለመጀመሪያ ጊዜ ለማስተናገድ እድል ማግኘቷን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። በዚህም መሠረት ውድድሩ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ይካሄዳል። የዓለም አትሌቲክስ የውድድር ዋና ዳይሬክተር ፒርስ ኦክላጋን በየካቲት ወር መጀመሪያ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል። የዓለም አትሌቲክስ የውድድር ዋና ዳይሬክተር ፒርስ ኦክላጋን የአትሌቲክስ መሰረተ ልማቶችን ጎበኙ በዚሁ ወቅትም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማዘጋጀት በቂ ዐቅም እንዳላት ገልጸው፤ የተለያዩ ውድድሮች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ እናደርጋለን ማለታቸው የሚታወስ ነው። ይህ ተከትሎም በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር በዓለም አትሌቲክስ ዓመታዊ መርሐ-ግብር ዛሬ ተካትቷል። ውድድሩን የዓለም አትሌቲክስ ከፍተኛ ባለሙያዎች የሚመሩት በመሆኑ፤ ለኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ሙያተኞች ልምድ ለማግኘት የሚያስችል ነው ተብሏል። ውድድሩ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ አትሌቶች የሚሳተፉበት ከመሆኑ ባሻገር አሸናፊ የሚሆኑ አትሌቶች ከፍተኛ ሽልማት እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል።
በተጠባቂው ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፋሲል ከነማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
Mar 4, 2026 93
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት ሲዳማ ቡና ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ካሜሮናዊው አጥቂ ብለሥ ናጎ በ92ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 42 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል። ከተከታዩ ነገሌ አርሲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነትም ወደ አምስት ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ 11ኛ ድሉንም አስመዝግቧል። በአንጻሩ በሊጉ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ፋሲል ከነማ በ33 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት አምስት ጨዋታዎች አላሸነፈም። በሌላኛው መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ቡና ባህርዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ቢኒያም ጌታቸው እና ዘላለም አባተ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮጵያ ቡና አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ29 ነጥብ ደረጃውን ከ11ኛ ወደ 7ኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱም ስምንተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ባህርዳር ከተማ በ27 ነጥብ ከነበረበት ስምንተኛ ደረጃ ወደ ዘጠነኛ ዝቅ ብሏል። ምሽት 12 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም፣ ወላይታ ድቻ ከሃዋሳ ከተማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በምስራቅ ሸዋ ዞን የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት ያደረጉ ችግኞች እየተዘጋጁ ነው
Mar 4, 2026 141
አዳማ ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት ያደረጉና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን የማፍላት ስራ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በምስራቅ ቦረና ዞን የእንስሳት መኖ እጥረት እንዳያጋጥም የመኖ ልማት ስራ ከተፋሰስ ጥበቃ ጋር ተቀናጅቶ እየተከናወነ ነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ሃገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ሐምሌ 2011 ዓ.ም መጀመሩ ይታወቃል። በምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና የጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዞኑ 11 ወረዳዎች ባሉ የችግኝ ማፊያ ጣቢያዎች ለመጪው ክረምት የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ተጀምሯል። ችግኝ ጣቢያዎቹ ለአረንጓዴ አሻራ ዘመቻው የተለያየ ዝርያ ያላቸው ችግኞችን አፍልቶ በማቅረብ ረገድ እያበረከቱ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰዋል። ዘንድሮም ለማዘጋጀት ከታቀደው ከ284 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥም 241 ነጥብ 4 ሚሊዮን ችግኞችን የማፍላት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። ቀሪ ችግኞችን የማፍላት ሥራም እስከ መጪው ግንቦት ወር ድረስ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በችግኝ ዝግጅቱም በአብዛኛው የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል ለሚያገለግሉ የደን እና ጥምር ደን ዝርያዎች ትኩረት የተሰጠ መሆኑን አስረድተዋል። በተጨማሪም ለአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን የሚያስገኙና እና ለምግብነት የሚውሉ 26 ነጥብ 7 ሚሊዮን የፍራፍሬ ችግኞችን ያካተተ የዘር ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል። የዘንድሮ ዓመት የችግኝ ተከላ የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት በማድረግ የሚከናወን መሆኑን ጠቁመው በዞኑ ባለፉት ዓመታት ከተተከሉ ችግኞች ከ85 በመቶ በላይ መጽደቃቸውን አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅትም የተተከሉ ችግኞችን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ የመጠበቅና የመንከባከብ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ነው ያረጋገጡት። በዘንድሮው ዓመት በዘርፉ የተቀመጠውን እቅድ ለማሳካትም የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ተቆፍረው መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል
Mar 3, 2026 152
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት እንደሚጠበቅባቸው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ገለጸ። "በምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የሚቋቋም ግብርናን ማስፋፋት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ቀጣናዊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በኢጋድ፣ የዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ፣ የሥርዓተ ምግብ ፕሮግራም ለምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ፣ የደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምርና ልማት ማስተባበሪያ ትብብር በተዘጋጀው መድረክም የግብርና ማሻሻያ ምክረ ሀሳቦችን እንደሚያፈልቅ ይጠበቃል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ተወካይ ዳህር ኤልሚ፤ በአየር ንብረትና በሥነ-ምኅዳር ደኅንነት የሚከሰት ለውጥ የግብርና ምርታማነት ላይ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለው የአፈር መራቆት፣ ድርቅ፣ ጎርፍ፣ ዝናብ እጥረትና በርሃማነት የምስራቅ አፍሪካ የግብርና ምርታማነትና የምግብ ፍጆታ ላይ አሉታዊ ጫና እንደሚያሳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የቀጣናው ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት ለመገንባት የቴክኖሎጂ፣ የግብዓትና የመረጃ ትንተና አቅም መገንባት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣንም የቀጣናውን ሀገራት የግብርና ምርታማነት የሚያሻሽል የአየር ሁኔታ የመረጃ ትንተና ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢኒስቲትዩት የተፈጥሮ ሃብትና የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም ፕሮግራም ዳይሬክተር አወቀ ሙሉዓለም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ሥርዓት ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችም የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ የአርሶና አርብቶ አደሩን የግብርና ምርታማነት እያሳደገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን፤ የግብርና ምርታማነት የሚያዘምኑ የፋይናንስና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በማስፋት የቀጣናው ሀገራት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር የኢጋድና የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦዌን በበኩላቸው፤ የግብርና ምርታማነትን ማረጋገጥ ለአፍሪካ ዕድገትና ብልጽግና ወሳኝ ነው ብለዋል። የቀጣናውንና አፍሪካን የግብርና ሥርዓት ለማዘመን በሚደረገው ጥረትም የኒውዝላንድ መንግስትና የልማት አጋሮች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች፣ ፖለሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችና ተመራማሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ስርጭትና መጠን ይጠናከራል
Mar 3, 2026 93
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦በቀጣዮቹ አስር ቀናት በሀገሪቱ የበልግ ሰብል አብቃይ አካባቢዎች የዝናብ መጠንና ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋና እየተጠናከረ እንደሚሄድ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ አራተኛውን የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ሊያስጀምር ነው በኢንስቲትዩቱ የሚቲዎሮሎጂ ትንበያ፣ምክር አገልግሎት እና ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አሳምነው ተሾመ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ለዝናብ መፈጠር ምቹ የሆኑ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ይበልጥ እየተጠናከሩ መሆናቸውን የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ። የዝናብ ስርጭቱ የሚሸፍናቸው ደቡብና ደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ (ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑ አካባቢዎች)፣ የስምጥ ሸለቆና አጎራባች አካባቢዎች፣ የመካከለኛውና የደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ምስራቅና ሰሜን ምስራቅ አካባቢዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። በእነዚህ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ የሚጠበቅ ሲሆን፣ በአብዛኛው ስፍራዎች የዝናብ መጠኑ መደበኛና ከመደበኛ በላይ እንደሚሆን ገልጸው፤አልፎ አልፎም ከባድ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል ተናግረዋል። የዝናቡ መሻሻል በተለይም ለበልግ አብቃይ አርሶ አደሮች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። በበልግ እየጣለ ያለው ዝናብ የማሳ ዝግጅትና ዘር፡ የአፈር እርጥበትን በማሻሻል አርሶ አደሩ የተለያዩ ሰብሎችን መዝራት እንዲችል ምቹ ሁኔታን በመፍጠር አዎንታዊ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። ለቋሚ ተክሎች፡ ቀደም ብለው ለተዘሩ የበልግ ሰብሎችና በአካባቢው ለሚገኙ ቋሚ ተክሎች ዕድገት ያለውን አስተዋጽኦም ገልጸዋል። ለውሃ አጠር አካባቢዎችም አርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ የሚጥለውን የዝናብ ውሃ በማሰባሰብና በማከማቸት ለቀጣይ እንዲጠቀም ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል። በበልግ የሚጥለው ዝናብ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የገጸ ምድር ውሃ መጠን በተለያዩ ተፋሰሶች ላይ እንደሚጨምርም ገልጸዋል። በዚህም ኦሞ ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ የላይኛውና መካከለኛው አዋሽ፣መካከለኛና ታችኛው አባይ፣ ገናሌ ዳዋ እና ዋቤ ሸበሌ ተፋሰሶች የተሻለ እርጥበት እንደሚያገኙ ይጠበቃል ብለዋል። በዚህም የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የውሃ ማጠራቀሚያዎችን በመጠቀም የውሃ መጠናቸው ከፍ እንዲል ያደርጋል ብለዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ የአገሪቱ ክፍሎች አሁንም ከፍተኛ የቀን ሙቀት እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በዚህም በጋምቤላ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝና ምዕራብ አማራ አካባቢዎች የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት ከ33 እስከ 37 ነጥብ 2 ዲግሪ ሴልሺየስ ሊደርስ እንደሚችል የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ተብሏል።
ኢንስቲትዩቱ አራተኛውን የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ሊያስጀምር ነው
Mar 3, 2026 100
ዳንቦያ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ከንባታ ዞን አራተኛውን ዘመናዊ የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳር የመትከል ተግባርን በማጠናቀቅ ስራ ለማስጀመር የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፈጠነ ተሾመ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ በክልሉ ከንባታ ዞን ዳንቦያ ወረዳ ዳቶ ዳርሀቦራ ተራራ ላይ ነው ዘመናዊ የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳሩን የተከለው። ራዳሩ በ250 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ያለን የአየር ሁኔታ መረጃ የመሰብሰብ አቅም ያለው ሲሆን፣ የትንተናና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥራዎችን በተሻለ ጥራት ለመከወን ያስችላል ብለዋል። በ14 ሜትር ከፍታ ላይ የተተከለው ይህ ራዳር የዝናብ መጠንን፣ የንፋስ ፍጥነትን፣ የዳመና እንቅስቃሴንና ዝናብ ያዘለ አውሎ ነፋስን የመሳሰሉ መረጃዎችን ከርቀት በመቃኘት ለዋናው የዳታ ማዕከል መረጃ ያስተላልፋል ብለዋል። ይህ የራዳር ጣቢያ በኢትዮጵያና በፊንላንድ መንግሥታት ድጋፍ 13 ሚሊዮን ዩሮ በሚጠጋ በጀት ወደ ሥራ ከሚገቡ ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ፤ አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ለማዘመንና የተሳለጠ መረጃ ለማቅረብ ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም አብራርተዋል። በፕሮጀክቱ የተጠቀሰውን ጨምሮ አራት የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳሮች፣ 10 የአየር ብክለት መከታተያ ጣቢያዎች፣ 10 የመብረቅ መከታተያና ሌሎች የተቀናጁ የሚቲዎሮሎጂ መሠረተ ልማትን የመገንባት ሥራን ያካተተ ነው ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ12 ስልታዊ ቦታዎች ላይ የራዳር ጣቢያዎችን ለመትከል እቅድ መያዙን ጠቁመው፤ አራተኛውን ጣቢያ በማጠናቀቅ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎቱን የማሳደግ አቅሙን አንደሚያጠናከር አስረድተዋል። ራዳሩ በተተከለበት አካባቢ የኃይል መቆራረጥም ሆነ የመረጃ ልውውጥ እንዳይቋረጥ የፀሐይ ብርሃን ኃይል (ሶላር ኢነርጂ) እየተገጠመ ይገኛል ብለዋል። የፕሮጀክቱን የመጨረሻ ምዕራፍ ለመጎብኘት በስፍራው የተገኙት በፊንላንድ ኤምባሲ የትብብር ዘርፍ ኃላፊ ቶሚ ሳርኪኦጃ መንግሥታቸው የኢትዮጵያን ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በመደገፉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የመንግሥታቱ ድርጅትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ ይገባል
Mar 4, 2026 107
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ እንደሚገባ ተገለጸ። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከጃፓን ኤምባሲ ጋር በመሆን የተባበሩት መንግሥታት ሪፎርም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል። የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ ቢሆኑም በተቋማዊ አወቃቀር ሥርዓት ላይ አፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ያገለሉ ናቸው። የአማኒ አፍሪካ ዳይሬክተር ሰለሞን አየለ ደርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት መዋቅር የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃ ሊወስድ ይገባል። በተቋማቱ የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥም ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ተከታታይ ሥራ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትና ከሌሎች ሀገራት ጋር ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን የዓለምአቀፍ ተቋማት ፍትሐዊ ውክልና ማስከበር የሚስችል መዋቅራዊ የሪፎርም እርምጃ እንዲወሰድ መስራት ይገባል ብለዋል። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በአፍሪካ ሕብረትና የአፍሪካ ዳያስፖራ ጉዳዮች ላይ በጥናትና ምርምር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የጋና አምባሳደር ሮበርት አፍሪይ(ዶ/ር)፤ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ያቀረበችው ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ችላ በመባሉ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ የሌላት ብቸኛ አህጉር አድርጓታል ብለዋል። ለዚህም የመንግስታቱ ድርጅት አፍሪካ በተሸከመችው የጸጥታው ምክር ቤት የሥራ ጫና ልክ ውክልና የሚያስገኛትን የሪፎርም እምርጃ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። በአፍሪካ ሕብረት የጃፓን ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኖቦሩ ሴኪጉቺ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በመንግስታቱ የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ላይ ፍትሐዊ ውክልና ሊሰጣት ይገባል ብለዋል። ጃፓንም አፍሪካ በመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የሚኖራትን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። ጃፓንና የጂ-4 አባል ሀገራት የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡም አስታውቀዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2024 በጸደቀው "የወደፊት ስምምነት" ላይ የጸጥታው ምክር ቤት መዋቅራዊ የማሻሻያ እርምጃ ለመወሰድ የተቀመጠው አቅጣጫ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቀጣናዊ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 1, 2026 137
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ እያሳደረ ባለው ከፍተኛ ተጽእኖ ምክንያት የቀጣናው የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እና የዜጎች የኑሮ መሰረት አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብ ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል።
የኢጋድ እና ተመድ ትብብር ለቀጣናዊ ሰላም
Feb 26, 2026 172
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ያላቸውን የጋራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የኢጋድ የደቡብ ሱዳን ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሙሳ ጃማ አሊ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። ልዩ ልዑኮቹ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት በተለይም በደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት የአምስት አባል ሀገራት ኮሚቴ (AU C5) እና ኢጋድ ያደረጉት የጋራ ጉባኤ የተገኙ ውጤቶች ላይም መክረዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ሰላም፣ መረጋጋት እና ቀጣናዊ ትብብር እውን እንዲሆን ያላቸውን ቅንጅት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ሩሲያ በትብብር መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
Feb 24, 2026 261
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ሩሲያ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ አጋርነት ዳይሬክተር ታትያና ዶቭጋሌንኮ ጋር በተቋሙ መቀመጫ ጅቡቲ ተወያይተዋል። በውይይቱ ወቅት ኢጋድ እና ሩሲያ በፖሊሲና ደኅንነት፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ ሳይንስ እና ትምህርት ዘርፎች ትብብር ማጎልበት የሚያስችላቸውን ስምምነት እና የድርጊት መርሐ-ግብር ተፈራርመዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ ጉዳዮች ተቀራርበው ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 169
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 236
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 251
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 693
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 265
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 370
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1114
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1091
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3588
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2394
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8193
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6676
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 357
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 351
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።