አርእስተ ዜና
ድራማዊ ክስተቶችን ባስተናገደው አስገራሚ ጨዋታ ፒኤስጂ ባየር ሙኒክን በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል
Jul 5, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ተጠባቂ መርሃ ግብር ፒኤስጂ ባየር ሙኒክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሜርሴዲስ-ቤንዝ ስታዲየም ዴዚሬ ዱዌ በ78ኛው እና ኡስማን ዴምቤሌ በ96ኛው ደቂቃ የማሸነፊያዋን ጎል አስቆጥረዋል። ጠንካራ ፉክክር በተደረገበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ለግብ የቀረቡ በርካታ እድሎች ፈጥረዋል። የፒኤስጂው ግብ ጠባቂ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ እና የባየር ሙኒክ ግብ ጠባቂ ማኑኤል ኖየር ግብ የሚሆኑ ኳሶችን በአስደናቂ ሁኔታ አድነዋል። የፒኤስጂ ተከላካዮች ዊሊያን ፓቾ እና ሉካስ ሄርናንዴዝ በፈጸመው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል። በጨዋታው ባየር ሙኒክ ሁለት ግቦችን አስቆጥረው ከጨዋታ ውጪ በመሆናቸው ተሽረዋል። በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ ፍጹም ቅጣት ምት አግኝቶም በቪዲዮ የታገዘ ዳኝነት (ቫር) ተሽሯል። በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ማብቂያ የባየርሙኒኩ የክንፍ ተጫዋች ጀማል ሙሲያላ ከፒኤስጂ ግብ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ ጋር በመጋጨቱ ምክንያት በግራ እግሩ ቁርጭምጭሚት ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዶ ተቀይሮ ወጥቷል። የተጫዋቹ አሰቃቂ ጉዳት በሁለቱ ቡድኖች ተጫዋቾች ከፍተኛ ድንጋጤ እና ፍርሃት ፈጥሮ ነበር። ሙሲያላ ወደ ሆስፒታል በማምራት ህክምናውን እየተከታተለ ይገኛል። ጉዳቱ ተጫዋቹን ለረጅም ጊዜ ከሜዳ ሊያርቀው ይችላል። ለ102 ደቂቃዎች የቆየው ጨዋታ አዝናኝ፣ ልብ አንጠልጣይ እና በክስተቶች የተሞላ ነበር። ውጤቱን ተከትሎ የአውሮፓ ሻምፒዮኑ ፒኤስጂ ለግማሽ ፍጻሜ አልፏል። ቡድኑ ከሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ አሸናፊ ጋር ይጫወታል። የመጨረሻው የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ በሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ መካከል ምሽት 5 ሰዓት ላይ በሜትላይፍ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
መገናኛ ብዙሃን ፍጥነትና ፈጠራ የታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ላይ አተኩረው ሊሰሩ ይገባል -አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ
Jul 5, 2025 58
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦የድህረ-እውነት ዘመን ተግዳሮቶችን ለመሻገር መገናኛ ብዙሃን ፍጥነትና ፈጠራ የታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ላይ አተኩረው ሊሰሩ እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ አስገነዘቡ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የዴሞክራሲ ተቋማት የሪፎርም ሥራቸውን በተመለከተ የጋራ ምክክር መድረክ አካሂደዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ በሚያደርግላቸው መገናኛ ብዙሃን ያሉ ችግሮችን በመጋፈጥ የተሻለ የይዘት ስራ እየሰሩ ናቸው። በመድረኩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የሥራ ሃላፊዎች የሪፎርም ሥራዎችን አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ተቋማዊ ሪፎርም አስመልክቶ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሠይፈ ደርቤ ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት፤ ኢዜአ ብሄራዊ ጥቅምን የማስጠበቅና ብሄራዊ መግባባትን የመፍጠር ተልዕኮውን በአግባቡ ለመወጣት የተለያዩ ተግባራትን አከናውኗል። የኢዜአ ማቋቋሚያ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ በሰው ሃይል፣ በአሰራርና አደረጃጀት ለይቶ ወደ ሥራ መግባቱንም አስታውሰዋል። ኢዜአ በአገር ውስጥና በውጭ ቋንቋዎች የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁና የአገር ገፅታ የሚገነቡ ጠንካራ የይዘት ስራዎችን እያሰራጨ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ተቋሙ በዲጂታል ሚዲያውም የኢትዮጵያን እውነትና መሻት የሚያንፀባርቁ ይዘቶችን ለአገር ውስጥና ለውጭ መገናኛ ብዙሃን ተደራሽ እያደረገ ነው ብለዋል። በአሁን ወቅትም በአምስት የአገር ውስጥና በሶስት የውጭ ቋንቋዎች የኢትዮጵያን ፍላጎት የሚያሳዩና ገፅታ የሚገነቡ መረጃዎችን ተደራሽ እየተደረገ ነው ብለዋል። ኢዜአ የተሰጠውን አገራዊ ተልዕኮ መወጣት የሚያስችለውን የህግና አሰራር ክፍተቶች ከመሙላት አኳያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላደረገውና እያደረገ ስላለው ድጋፍም አመስግነዋል። የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው፤ ኢቢሲ ችግሮችን በጥልቅ በመለየት ከአገራዊ ለውጡ በኋላ የይዘት፣ የገበያ፣ የቴክኖሎጂና የኮርፖሬት ሪፎርሞችን በማካሄድ ወደ ሥራ መግባቱን ተናግረዋል። በዚህም የፈጠራ ዘርፍ በማቋቋምና በክልል ያሉ ሃብቶችን ጥቅም ላይ ለማዋል የጀመራቸው ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን ነው የተናገሩት። ኢቢሲ ባሉት የቴሌቪዥን፣ የሬድዮና የዲጂታል አማራጮች ገዥ ትርክትን የሚያሰርፁ ጠንካራ የይዘት ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ መሳፍንት ተፈራ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ሚዲያው መስፋፋትን ተከትሎ በህትመት ውጤቶች ላይ የተጋረጡ ፈተናዎችን ለመሻገር የተለያዩ ሪፎርሞች መደረጋቸውን ነው ያብራሩት። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንደገለጹት፤ በድህረ እውነት ዘመን የሀሰተኛ እና የጥላቻ ንግግር ላይ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በዕውቀትና እውነት ላይ ተመስርቶ የሚሰራ መገናኛ ብዙሃን ያስፈልጋል። ምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ በሚያደርግላቸው መገናኛ ብዙሃን ያሉ ችግሮችን በመጋፈጥ የተሻለ የይዘት ስራ ለመስራት እያደረጉት ያሉውን ጥረት ያደነቁት አፈ ጉባዔው፤ የድህረ-እውነት ዘመን ተግዳሮቶችን ለመሻገር መገናኛ ብዙሃኑ ፍጥነትና ፈጠራ ለታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል። ምክር ቤቱም ለዴሞክራሲ ተቋማቱ ውጤታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው የገለጹት። የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ በበኩላቸው፤ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ መገናኛ ብዙሃን ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያለውን ቁልፍ ሚና በመረዳት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። በድህረ እውነት ዘመን የመገናኛ ብዙሃን ገዥ ትርክትን ለማስረፅ የጀመሩትን ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። ኢዜአ ከተመሰረተ ረጅም ዓመታት ቢያስቆጥርም በየጊዜው የሚያጋጥሙትን ፈተናዎች እየተሻገረ አሁን የደረሰበት ደረጃ በመድረሱ አድንቀዋል። በምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በመገናኛ ብዙሃን ላይ የነበሩ የአሰራርና አደረጃጀት ችግሮች በሂደት እየተፈቱ መምጣታቸውን ነው ያነሱት። ኢዜአ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፎ አስተማማኝ የዜና ምንጭ ለመሆን እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑንም ተናግረዋል።
ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ ለ174 መገናኛ ብዙሃን ህጋዊ ፍቃድ ተሰጥቷል
Jul 5, 2025 69
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ ለ174 መገናኛ ብዙሃን ፍቃድ መስጠቱን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ የተቋማዊ ሪፎርም ስራዎችን አፈጻጸም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና የዲሞክራሲያዊ ተቋማት የጋራ መድረክ ላይ ሪፖርት አቅርቧል።   የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናታን ተስፋዬ እንደገለጹት ባለስልጣኑ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅና የሚዲያ ነፃነትን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን ሰርቷል። የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃን ለመከላከል በአዋጅ የተሰጠውን ስልጣንና ኃላፊነት ለመወጣት በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን አብራርተዋል። ባለስልጣኑ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ መወጣት የሚያስችል የህግ ማሻሻያ ማድረጉንም እንዲሁ። ከለውጡ በፊት በዘርፉ የሚሰሩ የሙያና ሲቪክ ማህበራት ከስድስት የማይበልጡ እንደነበሩ አንስተው፤ አሁን ላይ ለውጡን ተከትሎ 38 ማህበራትና አደረጃጀቶች ወደ ስራ መግባታቸውንም ነው ያብራሩት። ከአገራዊ ለውጡ በኋላ በትምህርት በማህበረሰብ ሬዲዮ፣ በሃይማኖት፣ በቴሌቪዥንና በሬዲዮ እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ ላይ ፍቃድ ወስደው የሚሰሩ መገናኛ ብዙሃን ቁጥር መጨመሩንም ነው የገለጹት። በዚህም ከአገራዊ ለውጡ በኋላ 174 አዳዲስ መገናኛ ብዙሃን ከባለስልጣኑ ፍቃድ ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውን አብራርተዋል። የመገናኛ ብዙሃኑ የቋንቋ ተደራሽነትም ከነበረበት 39 አሁን ላይ ወደ 63 ከፍ ማለቱን አመልክተዋል።
መንግስት ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንቢያ ከፍተኛ ሀብት ከመመደብ ጀምሮ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል
Jul 5, 2025 58
ባሕርዳር፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንቢያና እድሳት ከፍተኛ ሀብት ከመመደብ ጀምር ለስፖርቱ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለጹ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የሚያዘጋጀው ስለኢትዮጵያ ምዕራፍ ሁለት፣7ኛ መድረክ "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር " በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በባሕርዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ተካሂዷል። በመድረኩ ማጠቃለያ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ጋር በባሕር ዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።     ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ በመድረኩ ማጠቃለያ እንዳመለከቱት፤ እንደ ሀገር በሌሎች ዘርፎች ላይ የታቀዱ ዕቅዶችን ለማሳካት ጠንካራና በስፖርት የዳበረ ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት ስፖርት ያለውን አስተዋጽኦና ሚና በመገንዘብ መንግስት ለዘርፉ ልማት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል።   ለዚህም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጀምሮ ከፍተኛ የሀገሪቱ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች በሄዱበት አካባቢ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በማበረታታት ድጋፍ እየሰጡ መሆኑን አንስተዋል። ስፖርት በተባበረ ክንድ ሀገርን ለመገንባትና ህብረብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር የሚያስችል እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሯ፤ ይህንን ከግምት ያስገቡ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ለዚህም መንግስት የስፖርትን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ከግምት ያስገባ ከታች ጀምሮ እስከ ፌደራል ድረስ ከፍተኛ የሆነ ሀብት በመመደብ ስፖርታዊ ውድድሮች እንዲጠናከሩ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንዲገነቡና እድሳት እንዲያገኙ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። "አሸናፊ ስነ-ልቦናና ሀገረ መንግስት ግንባታ"በሚል ርዕስ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ በበኩላቸው እንዳሉት፤ እንደመንግስት የስፖርት መሰረተ ልማት በመገንባት ከፍተኛ የሆነ ትኩረት ሰጥቷል።   ስፖርት የስፖርታዊ እንቅስቃሴ ብቻ ሳይሆን የሀገር መገንቢያ ኃይል አንዱ ትልቅ መሳሪያ ነው ተብሎ ተለይቶ እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል። የስፖርቱ ማህበረሰብ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ሚና እንዲኖረው የተደራጀ ስራ መከናወን እንዳለበት አመልክተዋል። ለዚህም ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አንስተው፤ ለዘርፉ እድገት ሚዲያውን ጨምሮ ሁሉም አካል የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል። ኢንስትራክተር አብረሃም መብራቱ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በአለም ኦሎምፒክ፣ በፊፋና በካፍ ተሰሚነት ያላቸው ትልልቅ ሰዎችን ያፈራች ሀገር ናት።   አሁን ላይ የክለቦች አወቃቀር ዘመናዊና ወቅታዊ ያለመሆንና የመልካም አስተዳደር ክፍተት እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቀ አለመሆን የዘርፉ መሰናክሎች መሆናቸውን አንስተዋል። እንደ ሀገር ለስፖርቱ በፖሊሲ ደረጃ የተሰጠው ትኩረት ከሌሎች አገራት የተሻለና ሊያሰራ የሚችል እንደሆነም አብራርተዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ጋር በባሕር ዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል። በመድረኩ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የስፖርት ባለሙያዎች፣አሰልጣኞችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን፤ ስፖርትን የተመለከተ አውደ ርዕይም ለእይታ ቀርቧል።  
የሚታይ
መገናኛ ብዙሃን ፍጥነትና ፈጠራ የታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ላይ አተኩረው ሊሰሩ ይገባል -አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ
Jul 5, 2025 58
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦የድህረ-እውነት ዘመን ተግዳሮቶችን ለመሻገር መገናኛ ብዙሃን ፍጥነትና ፈጠራ የታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ላይ አተኩረው ሊሰሩ እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ አስገነዘቡ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የዴሞክራሲ ተቋማት የሪፎርም ሥራቸውን በተመለከተ የጋራ ምክክር መድረክ አካሂደዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ በሚያደርግላቸው መገናኛ ብዙሃን ያሉ ችግሮችን በመጋፈጥ የተሻለ የይዘት ስራ እየሰሩ ናቸው። በመድረኩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የሥራ ሃላፊዎች የሪፎርም ሥራዎችን አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ተቋማዊ ሪፎርም አስመልክቶ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሠይፈ ደርቤ ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት፤ ኢዜአ ብሄራዊ ጥቅምን የማስጠበቅና ብሄራዊ መግባባትን የመፍጠር ተልዕኮውን በአግባቡ ለመወጣት የተለያዩ ተግባራትን አከናውኗል። የኢዜአ ማቋቋሚያ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ በሰው ሃይል፣ በአሰራርና አደረጃጀት ለይቶ ወደ ሥራ መግባቱንም አስታውሰዋል። ኢዜአ በአገር ውስጥና በውጭ ቋንቋዎች የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁና የአገር ገፅታ የሚገነቡ ጠንካራ የይዘት ስራዎችን እያሰራጨ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ተቋሙ በዲጂታል ሚዲያውም የኢትዮጵያን እውነትና መሻት የሚያንፀባርቁ ይዘቶችን ለአገር ውስጥና ለውጭ መገናኛ ብዙሃን ተደራሽ እያደረገ ነው ብለዋል። በአሁን ወቅትም በአምስት የአገር ውስጥና በሶስት የውጭ ቋንቋዎች የኢትዮጵያን ፍላጎት የሚያሳዩና ገፅታ የሚገነቡ መረጃዎችን ተደራሽ እየተደረገ ነው ብለዋል። ኢዜአ የተሰጠውን አገራዊ ተልዕኮ መወጣት የሚያስችለውን የህግና አሰራር ክፍተቶች ከመሙላት አኳያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላደረገውና እያደረገ ስላለው ድጋፍም አመስግነዋል። የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው፤ ኢቢሲ ችግሮችን በጥልቅ በመለየት ከአገራዊ ለውጡ በኋላ የይዘት፣ የገበያ፣ የቴክኖሎጂና የኮርፖሬት ሪፎርሞችን በማካሄድ ወደ ሥራ መግባቱን ተናግረዋል። በዚህም የፈጠራ ዘርፍ በማቋቋምና በክልል ያሉ ሃብቶችን ጥቅም ላይ ለማዋል የጀመራቸው ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን ነው የተናገሩት። ኢቢሲ ባሉት የቴሌቪዥን፣ የሬድዮና የዲጂታል አማራጮች ገዥ ትርክትን የሚያሰርፁ ጠንካራ የይዘት ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ መሳፍንት ተፈራ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ሚዲያው መስፋፋትን ተከትሎ በህትመት ውጤቶች ላይ የተጋረጡ ፈተናዎችን ለመሻገር የተለያዩ ሪፎርሞች መደረጋቸውን ነው ያብራሩት። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንደገለጹት፤ በድህረ እውነት ዘመን የሀሰተኛ እና የጥላቻ ንግግር ላይ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በዕውቀትና እውነት ላይ ተመስርቶ የሚሰራ መገናኛ ብዙሃን ያስፈልጋል። ምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ በሚያደርግላቸው መገናኛ ብዙሃን ያሉ ችግሮችን በመጋፈጥ የተሻለ የይዘት ስራ ለመስራት እያደረጉት ያሉውን ጥረት ያደነቁት አፈ ጉባዔው፤ የድህረ-እውነት ዘመን ተግዳሮቶችን ለመሻገር መገናኛ ብዙሃኑ ፍጥነትና ፈጠራ ለታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል። ምክር ቤቱም ለዴሞክራሲ ተቋማቱ ውጤታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው የገለጹት። የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ በበኩላቸው፤ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ መገናኛ ብዙሃን ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያለውን ቁልፍ ሚና በመረዳት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። በድህረ እውነት ዘመን የመገናኛ ብዙሃን ገዥ ትርክትን ለማስረፅ የጀመሩትን ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። ኢዜአ ከተመሰረተ ረጅም ዓመታት ቢያስቆጥርም በየጊዜው የሚያጋጥሙትን ፈተናዎች እየተሻገረ አሁን የደረሰበት ደረጃ በመድረሱ አድንቀዋል። በምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በመገናኛ ብዙሃን ላይ የነበሩ የአሰራርና አደረጃጀት ችግሮች በሂደት እየተፈቱ መምጣታቸውን ነው ያነሱት። ኢዜአ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፎ አስተማማኝ የዜና ምንጭ ለመሆን እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑንም ተናግረዋል።
ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ ለ174 መገናኛ ብዙሃን ህጋዊ ፍቃድ ተሰጥቷል
Jul 5, 2025 69
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ ለ174 መገናኛ ብዙሃን ፍቃድ መስጠቱን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ የተቋማዊ ሪፎርም ስራዎችን አፈጻጸም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና የዲሞክራሲያዊ ተቋማት የጋራ መድረክ ላይ ሪፖርት አቅርቧል።   የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናታን ተስፋዬ እንደገለጹት ባለስልጣኑ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅና የሚዲያ ነፃነትን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን ሰርቷል። የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃን ለመከላከል በአዋጅ የተሰጠውን ስልጣንና ኃላፊነት ለመወጣት በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን አብራርተዋል። ባለስልጣኑ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ መወጣት የሚያስችል የህግ ማሻሻያ ማድረጉንም እንዲሁ። ከለውጡ በፊት በዘርፉ የሚሰሩ የሙያና ሲቪክ ማህበራት ከስድስት የማይበልጡ እንደነበሩ አንስተው፤ አሁን ላይ ለውጡን ተከትሎ 38 ማህበራትና አደረጃጀቶች ወደ ስራ መግባታቸውንም ነው ያብራሩት። ከአገራዊ ለውጡ በኋላ በትምህርት በማህበረሰብ ሬዲዮ፣ በሃይማኖት፣ በቴሌቪዥንና በሬዲዮ እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ ላይ ፍቃድ ወስደው የሚሰሩ መገናኛ ብዙሃን ቁጥር መጨመሩንም ነው የገለጹት። በዚህም ከአገራዊ ለውጡ በኋላ 174 አዳዲስ መገናኛ ብዙሃን ከባለስልጣኑ ፍቃድ ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውን አብራርተዋል። የመገናኛ ብዙሃኑ የቋንቋ ተደራሽነትም ከነበረበት 39 አሁን ላይ ወደ 63 ከፍ ማለቱን አመልክተዋል።
መንግስት ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንቢያ ከፍተኛ ሀብት ከመመደብ ጀምሮ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል
Jul 5, 2025 58
ባሕርዳር፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንቢያና እድሳት ከፍተኛ ሀብት ከመመደብ ጀምር ለስፖርቱ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለጹ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የሚያዘጋጀው ስለኢትዮጵያ ምዕራፍ ሁለት፣7ኛ መድረክ "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር " በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በባሕርዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ተካሂዷል። በመድረኩ ማጠቃለያ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ጋር በባሕር ዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።     ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ በመድረኩ ማጠቃለያ እንዳመለከቱት፤ እንደ ሀገር በሌሎች ዘርፎች ላይ የታቀዱ ዕቅዶችን ለማሳካት ጠንካራና በስፖርት የዳበረ ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት ስፖርት ያለውን አስተዋጽኦና ሚና በመገንዘብ መንግስት ለዘርፉ ልማት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል።   ለዚህም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጀምሮ ከፍተኛ የሀገሪቱ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች በሄዱበት አካባቢ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በማበረታታት ድጋፍ እየሰጡ መሆኑን አንስተዋል። ስፖርት በተባበረ ክንድ ሀገርን ለመገንባትና ህብረብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር የሚያስችል እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሯ፤ ይህንን ከግምት ያስገቡ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ለዚህም መንግስት የስፖርትን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ከግምት ያስገባ ከታች ጀምሮ እስከ ፌደራል ድረስ ከፍተኛ የሆነ ሀብት በመመደብ ስፖርታዊ ውድድሮች እንዲጠናከሩ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንዲገነቡና እድሳት እንዲያገኙ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። "አሸናፊ ስነ-ልቦናና ሀገረ መንግስት ግንባታ"በሚል ርዕስ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ በበኩላቸው እንዳሉት፤ እንደመንግስት የስፖርት መሰረተ ልማት በመገንባት ከፍተኛ የሆነ ትኩረት ሰጥቷል።   ስፖርት የስፖርታዊ እንቅስቃሴ ብቻ ሳይሆን የሀገር መገንቢያ ኃይል አንዱ ትልቅ መሳሪያ ነው ተብሎ ተለይቶ እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል። የስፖርቱ ማህበረሰብ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ሚና እንዲኖረው የተደራጀ ስራ መከናወን እንዳለበት አመልክተዋል። ለዚህም ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አንስተው፤ ለዘርፉ እድገት ሚዲያውን ጨምሮ ሁሉም አካል የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል። ኢንስትራክተር አብረሃም መብራቱ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በአለም ኦሎምፒክ፣ በፊፋና በካፍ ተሰሚነት ያላቸው ትልልቅ ሰዎችን ያፈራች ሀገር ናት።   አሁን ላይ የክለቦች አወቃቀር ዘመናዊና ወቅታዊ ያለመሆንና የመልካም አስተዳደር ክፍተት እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቀ አለመሆን የዘርፉ መሰናክሎች መሆናቸውን አንስተዋል። እንደ ሀገር ለስፖርቱ በፖሊሲ ደረጃ የተሰጠው ትኩረት ከሌሎች አገራት የተሻለና ሊያሰራ የሚችል እንደሆነም አብራርተዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ጋር በባሕር ዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል። በመድረኩ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የስፖርት ባለሙያዎች፣አሰልጣኞችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን፤ ስፖርትን የተመለከተ አውደ ርዕይም ለእይታ ቀርቧል።  
በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት 63 ሚሊዮን ዜጎች ተጠቃሚ ሆነዋል
Jul 5, 2025 51
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በ2017 በጀት ዓመት የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ ዜጎች ቁጥር 63 ሚሊዮን መድረሱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የምግብና ሥርዓት ምግብ እንዲሁም የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚሁ ወቅት፥ ስርዓተ ምግብን ማሻሻል ጤናማና አምራች ትውልድ ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የምግብና ስርዓተ ምግብ የ10 ዓመት ስትራቴጂና የሰቆጣ ቃልኪዳን ማስፋፊያ ምዕራፍ ባለፉት አራት ዓመታት ተስፋ ሰጪ በሆነ መንገድ እየተተገበሩ መሆኑን አንስተዋል። በሰቆጣ ቃልኪዳን በማስፋፋት ምዕራፍ ትግበራው በ2017 በጀት ዓመት በ334 ወረዳዎች መተግበሩን ተናግረዋል። በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሚያጠቡና ነፍሰጡር እናቶች እንዲሁም ህጻናት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሰቆጣ ቃል ኪዳን አበርክቶን ለማሳደግ በ2018 ዓ.ም የሚተገበርባቸውን ወረዳዎች 520 ለማድረስ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። በቃልኪዳኑ መሠረት በ2022 ዓ.ም መቀንጨርን ዜሮ ለማድረግ የምግብና ስርዓተ ምግብ ተግባራትን ሽፋን ማሳደግ እንዲሁም በቂ ሀብት መመደብ ላይ በሁሉም ክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ተመሳሳይ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባው አንስተዋል። ሥርዓተ ምግብን ለማሻሻልና ሀገራዊ የጤና ግቦችን ለማሳካት የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሻራ እና ሌሎች ኢኒሼቲቮች ወሳኝ ሚና እያበረከቱ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሁሉን አቀፍ የጤና ተደራሽነትን እውን ለማድረግ የማይበገር የጤና ስርዓት በመገንባትና የጤና መሰረተ ልማትን በማስፋት የጤና አገልግሎት ሽፋንን ከ95 በመቶ በላይ ማድረስ ተችሏል ነው ያሉት። የጤና መድህን ስትራቴጂ መክፈል የማይችሉ ዜጎችን የጤና ዋስትና ለማሳደግ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት እየተተገበረ መሆኑን ገልጸዋል። የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ሽፋን በ2017 በጀት ዓመት ወደ 1ሺህ 195 ወረዳዎች ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል። በዚህም 63 ሚሊዮን ዜጎች በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን መርሃግብር ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ አንስተዋል። ይህም የተሳካው በሁሉም ክልሎች የመክፈል አቅምን መሰረት ያደረገ አሰራር በመተግበሩ ነው ብለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ ለ174 መገናኛ ብዙሃን ህጋዊ ፍቃድ ተሰጥቷል
Jul 5, 2025 69
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ ለ174 መገናኛ ብዙሃን ፍቃድ መስጠቱን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ የተቋማዊ ሪፎርም ስራዎችን አፈጻጸም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና የዲሞክራሲያዊ ተቋማት የጋራ መድረክ ላይ ሪፖርት አቅርቧል።   የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናታን ተስፋዬ እንደገለጹት ባለስልጣኑ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅና የሚዲያ ነፃነትን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን ሰርቷል። የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃን ለመከላከል በአዋጅ የተሰጠውን ስልጣንና ኃላፊነት ለመወጣት በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን አብራርተዋል። ባለስልጣኑ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ መወጣት የሚያስችል የህግ ማሻሻያ ማድረጉንም እንዲሁ። ከለውጡ በፊት በዘርፉ የሚሰሩ የሙያና ሲቪክ ማህበራት ከስድስት የማይበልጡ እንደነበሩ አንስተው፤ አሁን ላይ ለውጡን ተከትሎ 38 ማህበራትና አደረጃጀቶች ወደ ስራ መግባታቸውንም ነው ያብራሩት። ከአገራዊ ለውጡ በኋላ በትምህርት በማህበረሰብ ሬዲዮ፣ በሃይማኖት፣ በቴሌቪዥንና በሬዲዮ እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ ላይ ፍቃድ ወስደው የሚሰሩ መገናኛ ብዙሃን ቁጥር መጨመሩንም ነው የገለጹት። በዚህም ከአገራዊ ለውጡ በኋላ 174 አዳዲስ መገናኛ ብዙሃን ከባለስልጣኑ ፍቃድ ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውን አብራርተዋል። የመገናኛ ብዙሃኑ የቋንቋ ተደራሽነትም ከነበረበት 39 አሁን ላይ ወደ 63 ከፍ ማለቱን አመልክተዋል።
ኮሌጁ ከወዳጅ ሀገራት ጋር ያለውን ወታደራዊ ትብብር እና ዲፕሎማሲ እንዲጠናከር አስተዋጽኦ እያደረገ ነው
Jul 5, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ከወዳጅ ሀገራት የመጡ ወታደራዊ አመራሮችን በማሰልጠን ወታደራዊ ትብብርና ዲፕሎማሲ እንዲጠናከር አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን ተናገሩ። የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ የ15ኛ ዙር መደበኛ ኮርስ ከፍተኛ መኮንኖችን አስመርቋል።     በመርኃ ግብሩ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን እና የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሙሉጌታ አምባቸው፣ ጄኔራል መኮንኖች፣ ወታደራዊ አታሼዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን በዚሁ ወቅት፤ በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ላጠናቀቁ ተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። ተመራቂዎቹ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የተሃድሶ ሂደት ውጤት መሆናቸውን ተናግረው፤ ይህም የመከላከያ ስትራቴጂካዊ አመራር ቁርጠኝነትና ራዕይም ማሳያ እንደሆነ ገልፀዋል።   ከወዳጅ ሀገራት የመጡ ወታደራዊ አመራሮችን አሰልጥኖ በማስመረቁ በሀገራት መካከል ለሚኖረው ትብብር እና ወታደራዊ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል። የወዳጅ ሀገር ተመራቂዎች በኢትዮጵያ እና በሀገራቸው መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሰሩ አደራ ብለዋል። የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሙሉጌታ አምባቸው በበኩላቸው፤ ኮሌጁ የአፍሪካ እህት ሃገራት መኮንኖች ስልጠና መስጠቱን ተናግረዋል።   ኮሌጁ ከስልጠናው ባሻገር ለቀጣናዊ ትብብር ዘላቂ መሠረት የሚሆን ወዳጅነት መገንባት መቻሉን ጄኔራሉ ተናግረዋል። ከኬንያ የመጣችውና ትምህርቷን ተከታትላ የተመረቀችው ሌተናል ኮሎኔል ሀዋ ሀድጃ አይዛክ የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ በአፍሪካ ሀገራት ትብብርና ወዳጅነት የሚያጠናክር ተግባር እያከናወነ ይገኛል ብላለች።   በኮሌጁ በነበራት ቆይታ ሙያዋን በተሻለ መልኩ መፈፀም የሚያስችል እውቀት ማግኘቷን ተናግራለች። ስልጠናው በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል እንደሆነ የተናገረው ከሩዋንዳ የመጣው ሜጀር ጆን ኬነዲ ንዲዛዬ ነው።  
መንግስት ለሰላም ያለው የማይናወጥ አቋም የሚደነቅ ነው
Jul 5, 2025 67
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦መንግስት ለሰላም ያለው የማይናወጥ አቋም የሚደነቅ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሄዷል፡፡ በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸው ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ውስጥ ተከስተው የነበሩ ግጭቶች ተፈትተው አሁን ላይ አንጻራዊ ሰላም ሰፍኗል ብለዋል። መንግስት በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች በተሳሳተ ስሌት ነፍጥ አንግበው ከሚንቀሳቀሱ ሃይሎች ጋር ለመነጋገር አሁንም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ ማብራሪያውን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች አስተያየታቸውን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል መምበረ አግዘው እንዳሉት መንግስት ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የልማት ተግባራትን በማከናወን የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዚህም በአገሪቱ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ያለው የማይናወጥ አቋም የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተሳሳተ መንገድ ወደ ሰላም ያልመጡ ራሳቸውን ለውይይት ዝግጁ ማድረግ እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አለማየሁ ታዬ እንዳሉት ግጭት ያለንበትን ዘመን የማይመጥን፣ ዘርፈ ብዙ ጉዳት የሚያስከትል እንጂ ዘላቂ ሰላምና ልማትን የሚያረጋግጥ አይደለም ብለዋል፡፡ በመሆኑም በተሳሳተ ስሌት ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለምክክር መዘጋጀት እንዳለባቸው ሃሳባቸውን ሰጥተዋል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋሉ ግጭቶች በዘለቂነት ቢቋጩ የነዋሪውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆኑን አዲስ አበባ ምስክር ናት ያሉት አስተያየት ሰጪ ደግሞ ወይዘሮ ብርቄ ገብረ ዮሐንስ ናቸው፡፡ በመሆኑም ሁሉም ዜጋ ለሰላም በጋራ መስራት እንዳለበት ነው ያነሱት፡፡  
የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተደራሽነት ለማስፋት በቴክኖሎጂ የታገዘ ሥራ እየተከናወነ ነው
Jul 5, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦ሰባተኛውን ዙር ጠቅላላ ምርጫ ግልፅነትና ተደራሽነት ለማስፋት በቴክኖሎጂ የታገዘ ሥራ እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የሆኑ የዴሞክራሲ ተቋማት የሪፎርም ስራቸውን አስመልክቶ የጋራ የውይይት መድረክ እያካሄዱ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ የተቋማቸውን የሪፎርም ስራዎች አስመልክቶ ሪፖርት አቅርበዋል። በዚሁ ጊዜ ቦርዱ በህዝብና በመንግስት የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የነበሩበትን የአሰራር ክፍተቶች ለይቶ ለመፍትሄው ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል። በዚህም በህግና በአሰራር፣ በሰው ሃይልና አደረጃጀት ያሉ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ሪፎርም ማድረጉንም አመልክተዋል። ካለፉት ምርጫ ሂደቶች የተሻሉ ተሞክሮዎችን በመውሰድና ችግሮችን በመለየት ለቀጣዩ ምርጫ የበለጠ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ነው ያብራሩት። የሰባተኛውን ዙር ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒነት ያለው እንዲሆን በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ለመተግበር ዝግጅት እያደረገን ነው ብለዋል። በዚህም የምርጫ ሂደቱን ፈጣንና ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ የሞባይል መተግበሪያ በማበልፀግ የዕጩዎችንና የመራጮችን ምዝገባ በቴክኖሎጂ ለማከናወን ስራዎች ተጀምረዋል ነው ያሉት። ተቋሙ ነፃና ገለልተኛ ሆኖ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት በሰው ሃይልና በአደረጃጀት ራሱን ማብቃት የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የዕጩዎችና የመራጮችን ምዝገባ ለማካሄድ የሚያግዘው ቴክኖሎጂ አስተማማኝና በቦርዱ ባለሙያዎች የበለፀገ ሲስተም መሆኑንም ገልጸዋል። ምዝገባው በሞባይል መተግበሪያ፣ በቦርዱ ባለሙያዎች እገዛ እንዲሁም በማኑዋል መንገድ እንደሚከናወንም አመልክተዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችና መራጮች ስለ ቴክኖሎጂው አጠቃቀም በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እገዛ ይደረግላቸዋል ብለዋል። ለዚህ አሰራር የሚሆን አዋጅ ለምክር ቤቱ መቅረቡንም ነው ያመለከቱት። የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ዋና ዕምባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በበኩላቸው፤ ተቋሙ የተጣለበትን ኃላፊነት መወጣት የሚያስችለውን ሪፎርም ሲያከናውን ነበር ብለዋል። በዚህም አስተዳደራዊ በደሎችን መፍታት የሚያስችሉ የሰው ሃይልና አደረጃጀት መፍጠሩን በማንሳት።   በተያዘው በጀት ዓመት 11ወራት ከ2ሺ በላይ አቤቱታዎችን መርምሮ የውሳኔ ሀሳብ መስጠቱን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ፤ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ላይ የሚደርሱ ጥሰቶችን ማረም የሚያስችሉ ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት ተዘርግቶ ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል።   በተለይም የሰብዓዊ መብቶች ተጥሰዋል የሚሉ አቤቱታዎች ሲቀርቡ በሁለቱም ወገን ያለውን እውነታ በማጣራት ፍትሃዊና ትክክለኛ ሪፖርት እንዲወጣና ጥሰቱ እንዲታረም እየሰራ ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መተግበሩንም ጠቅሰው፤ የሰብዓዊ መብት አያያዝና አጠባበቅ የበለጠ እንዲጠናከር የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።  
መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ዘርፍ የተደራጀና ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ በአስተሳሰብና ሥነ-ልቦና የተገነባ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Jul 5, 2025 77
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ዘርፍ በወጉ የተደራጀ፣ ዘመኑን የዋጀ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ በአስተሳሰብና ሥነ-ልቦና የተገነባ ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ የ15ኛ ዙር መደበኛ ኮርስ ከፍተኛ መኮንኖችን አስመርቋል። በመርኃ ግብሩ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን እና የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሙሉጌታ አምባቸው፣ ጄኔራል መኮንኖች፣ ወታደራዊ አታሼዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።   የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኮሌጁ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም የመከላከያ ሠራዊት ክፍሎችና ኃይሎች ውስጥ በብቃት የመምራት ችሎታ ያላቸውን ከፍተኛ ታክቲካል የጦር ክፍሎችን፣ የኦፕሬሽናል ውጊያ ሳይንስና ጥበብ ሥልጠና የወሰዱ በርካታ ከፍተኛ መኮንኖች ማፍራቱን ተናግረዋል። በዚህ ዓመትም በኮሌጁ ስልጠና በመውሰድ በብቃት አጠናቀው ለምረቃ የበቁ ከፍተኛ መኮንኖች የመከላከያ ሠራዊት እያስመዘገበ ያለውን ብቁ የሰለጠነ ፕሮፌሽናል ሠራዊት የመገንባት ጥረት ውጤት መሆናቸውን ጠቅሰዋል። አገራዊ እና ተቋማዊ ሪፎርም ከተበሰረበት ጊዜ ጀምሮም ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገበች እንደምትገኝ ተናግረዋል። በመከላከያ ተቋማዊ ግንባታ መስክ ከፍተኛ ለውጥ እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው፤ ውጤቱ በቁርጠኛ የመንግስት አመራርና ፅናትን በተላበሱ የሠራዊት አዛዦችና በጀግናው ሠራዊታችን መስዋዕትነት ነው ብለዋል። የመከላከያ ሠራዊቱን ፕሮፌሽናል በማድረግና በማዘመን በቀጣይ ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶችን ከሩቅ የማስቀረት እንዲሁም ብሔራዊ አደጋ ቢከሰት በአስተማማኝ መቀልበስ የሚችል አቅም ያለው ሠራዊት ገንብተናል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ዘርፍ ተለውጦ በወጉ የተደራጀ፣ ዘመኑን የዋጀ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ በአስተሳሰብና ሥነ-ልቦና የተገነባ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም የወታደራዊ ስትራቴጂ ኦፕሬሽን፣ ስልታዊ ጥበብና እውቀትን የተላበሰና ኢትዮጵያን የሚመጥን የአገር መከላከያ ለመገንባት የተቀመጠውን ስትራቴጂ ለማሳካት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።   ተመራቂ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችም በመከላከያ አዛዥና ስታፍ ኮሌጅ በነበራቸው ቆይታ ያገኙትን ትምህርት፣ የተሟላ እውቀት፤ ክህሎትና አስተሳሰብ በመጠቀም ለዚህ አቅም መሆን አለባቸው ብለዋል። ተመራቂዎች በሚሰማሩባቸው የሠራዊቱ ክፍሎች የወታደራዊ ሥነ-ምግባር፣ የግዳጅ አፈፃፀም ብቃትና የማይናወጥ ሥነ-ልቦና ተምሳሌትና አርዓያ በመሆን እንዲያገለግሉ አስገንዝበዋል። ኮሌጁ የኢትዮጵያን መከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች ከማብቃት ባሻገር ከወዳጅ አገራት የመጡ ከፍተኛ መኮንኖችን ተቀብሎ በማስተማርና በማሰልጠን ወታደራዊ ትብብርና ዲፕሎማሲ ይበልጥ እንዲጠናከር በማድረግ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል ፡፡   በዛሬው ዕለትም ከበርካታ ወዳጅ አገሮች የመጡ ከፍተኛ መኮንኖች በኮሌጁ ሲሰጥ የቆየውን ትምህርት አጠናቀው ለምረቃ መብቃታቸውን አንስተዋል። ተመራቂ የወዳጅ አገሮች ከፍተኛ መኮንኖች በነበራችው ቆይታ ያገኙትን አቅምና ዕውቀት ለአገራቸው ተልዕኮ እንዲጠቀሙበት ያስገነዘቡት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ፤ ስልጠና የሰጠቻቸውን ኢትዮጵያ ከአገራቸው ጋር ለጠበቀ ወዳጅነት መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ይህ የትምህርትና ስልጠና ትብብርም በአገሮች መካከል ሊኖር የሚችልን ወታደራዊ ዲፕሎማሲ ወደ ከፍተኛ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ጠቅሰው ይህንንም አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
የኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመደራደር አቅም እየጎለበተ መጥቷል - የምክር ቤት አባላት
Jul 5, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመደራደር አቅም በተጨባጭ አየጎለበተ መምጣቱን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2017 በጀት ዓመት የመንግስትን የሥራ አፈጻጸምን አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወሳል። በዚሁ ወቅት ባለፉት ሰባት ዓመታት አገሪቷ ምንም ዓይነት ኮሜርሺያል (ከፍተኛ ወለድ ያለው) ብድር አለመውሰዷን ነው የገለጹት። ይሁን እንጂ ባለፉት መንግስታት የተከማቸ የውጭ ዕዳ ለመክፈል ከፍተኛ ጥረት ስታደርግና የብድር መክፈያ ጊዜውን ለማራዘም ስትደራደር መቆየቷን አብራርተዋል። በዚህም ባለፉት አራት ዓመታት ከተለያዩ መንግስታት ጋር በተደረገ ድርድር የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ ሽግሽግ መደረጉንም ነው ያነሱት። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል ነው ብለዋል። ብድር ለታለመለት ዓላማ ካልዋለ ለትውልድ ዕዳ መሆኑ እንደማይቀር ጠቁመው፤ መንግስት ይህን ዕዳ ለማቃለል እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎችንም አድንቀዋል። ረዳት ፕሮፌሰር ገነነ ገደቦ መንግስት ከተለያዩ አገራት የሚወስዳቸው ብድሮች ለታለመላቸው ዓላማ ማዋልና ብድሩን በጊዜ መመለስ ይገባል ይላሉ።   በከፍተኛ ወለድ የመጡ ብድሮች አገርና ትውልድ ላይ ጫና የሚፈጥሩና ተጨማሪ ልማት እንዳይኖር የሚያደርጉ በመሆኑ መንግስት በድርድር ዕዳውን ማሸጋሸጉ ተገቢ መሆኑንም አንስተዋል። ሌላዋ የምክር ቤት አባል ነጃት ግርማ (ዶ/ር)፤ ቀደም ሲል አገሪቷን ሲመሩ የነበሩ መንግስታት ለትውልዱ ከፍተኛ ዕዳ አሸጋግረዋል ነው ያሉት። ከለውጡ ዓመታት በኋላ መንግስት ይህን የትውልድ ዕዳ ለማቃለል እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎችንም አድንቀዋል።   የተለያዩ መንግስታት የኢትዮጵያን ዕዳ ለማሸጋሸግ ያሳዩት ፍላጎትም አገሪቷ በራሷ ለመልማት ያላትን አቋም ከማየት የመነጨ መሆኑን በማንሳት። ሌላው የምክር ቤት አባል ፈትህ መህዲ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት ምንም ዓይነት ከፍተኛ ወለድ ያለው ኮሜርሺያል ብድር አለመውሰዷ ዕዳዋን የመቀነስ ፍላጎቷን ያሳያል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፤ አገሪቷ ቀደም ሲል የወሰደቻቸው ብድሮች የእፎይታ ጊዜ ለማግኘት የተደረገው ሽግሽግ የአገሪቷን የመደራደር አቅም መጎልበት ያሳያል።   የምክር ቤቱ አባል ሰሚራ የሱፍም በዚህ ሀሳብ ይስማማሉ። የዕዳ ሽግሽጉም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያ ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነት መጠናከር የሚያሳይ ነው ብለዋል። ምክር ቤቱ የሚቀርቡለት የብድር ስምምነቶች ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ በአግባቡ በመፈተሽ እንደሚያጸድቅም ነው አባላቱ የገለጹት።
ፖለቲካ
ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ ለ174 መገናኛ ብዙሃን ህጋዊ ፍቃድ ተሰጥቷል
Jul 5, 2025 69
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ ለ174 መገናኛ ብዙሃን ፍቃድ መስጠቱን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ የተቋማዊ ሪፎርም ስራዎችን አፈጻጸም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና የዲሞክራሲያዊ ተቋማት የጋራ መድረክ ላይ ሪፖርት አቅርቧል።   የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናታን ተስፋዬ እንደገለጹት ባለስልጣኑ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅና የሚዲያ ነፃነትን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን ሰርቷል። የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃን ለመከላከል በአዋጅ የተሰጠውን ስልጣንና ኃላፊነት ለመወጣት በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን አብራርተዋል። ባለስልጣኑ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ መወጣት የሚያስችል የህግ ማሻሻያ ማድረጉንም እንዲሁ። ከለውጡ በፊት በዘርፉ የሚሰሩ የሙያና ሲቪክ ማህበራት ከስድስት የማይበልጡ እንደነበሩ አንስተው፤ አሁን ላይ ለውጡን ተከትሎ 38 ማህበራትና አደረጃጀቶች ወደ ስራ መግባታቸውንም ነው ያብራሩት። ከአገራዊ ለውጡ በኋላ በትምህርት በማህበረሰብ ሬዲዮ፣ በሃይማኖት፣ በቴሌቪዥንና በሬዲዮ እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ ላይ ፍቃድ ወስደው የሚሰሩ መገናኛ ብዙሃን ቁጥር መጨመሩንም ነው የገለጹት። በዚህም ከአገራዊ ለውጡ በኋላ 174 አዳዲስ መገናኛ ብዙሃን ከባለስልጣኑ ፍቃድ ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውን አብራርተዋል። የመገናኛ ብዙሃኑ የቋንቋ ተደራሽነትም ከነበረበት 39 አሁን ላይ ወደ 63 ከፍ ማለቱን አመልክተዋል።
ኮሌጁ ከወዳጅ ሀገራት ጋር ያለውን ወታደራዊ ትብብር እና ዲፕሎማሲ እንዲጠናከር አስተዋጽኦ እያደረገ ነው
Jul 5, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ከወዳጅ ሀገራት የመጡ ወታደራዊ አመራሮችን በማሰልጠን ወታደራዊ ትብብርና ዲፕሎማሲ እንዲጠናከር አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን ተናገሩ። የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ የ15ኛ ዙር መደበኛ ኮርስ ከፍተኛ መኮንኖችን አስመርቋል።     በመርኃ ግብሩ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን እና የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሙሉጌታ አምባቸው፣ ጄኔራል መኮንኖች፣ ወታደራዊ አታሼዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን በዚሁ ወቅት፤ በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ላጠናቀቁ ተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። ተመራቂዎቹ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የተሃድሶ ሂደት ውጤት መሆናቸውን ተናግረው፤ ይህም የመከላከያ ስትራቴጂካዊ አመራር ቁርጠኝነትና ራዕይም ማሳያ እንደሆነ ገልፀዋል።   ከወዳጅ ሀገራት የመጡ ወታደራዊ አመራሮችን አሰልጥኖ በማስመረቁ በሀገራት መካከል ለሚኖረው ትብብር እና ወታደራዊ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል። የወዳጅ ሀገር ተመራቂዎች በኢትዮጵያ እና በሀገራቸው መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሰሩ አደራ ብለዋል። የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሙሉጌታ አምባቸው በበኩላቸው፤ ኮሌጁ የአፍሪካ እህት ሃገራት መኮንኖች ስልጠና መስጠቱን ተናግረዋል።   ኮሌጁ ከስልጠናው ባሻገር ለቀጣናዊ ትብብር ዘላቂ መሠረት የሚሆን ወዳጅነት መገንባት መቻሉን ጄኔራሉ ተናግረዋል። ከኬንያ የመጣችውና ትምህርቷን ተከታትላ የተመረቀችው ሌተናል ኮሎኔል ሀዋ ሀድጃ አይዛክ የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ በአፍሪካ ሀገራት ትብብርና ወዳጅነት የሚያጠናክር ተግባር እያከናወነ ይገኛል ብላለች።   በኮሌጁ በነበራት ቆይታ ሙያዋን በተሻለ መልኩ መፈፀም የሚያስችል እውቀት ማግኘቷን ተናግራለች። ስልጠናው በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል እንደሆነ የተናገረው ከሩዋንዳ የመጣው ሜጀር ጆን ኬነዲ ንዲዛዬ ነው።  
መንግስት ለሰላም ያለው የማይናወጥ አቋም የሚደነቅ ነው
Jul 5, 2025 67
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦መንግስት ለሰላም ያለው የማይናወጥ አቋም የሚደነቅ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሄዷል፡፡ በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸው ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ውስጥ ተከስተው የነበሩ ግጭቶች ተፈትተው አሁን ላይ አንጻራዊ ሰላም ሰፍኗል ብለዋል። መንግስት በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች በተሳሳተ ስሌት ነፍጥ አንግበው ከሚንቀሳቀሱ ሃይሎች ጋር ለመነጋገር አሁንም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ ማብራሪያውን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች አስተያየታቸውን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል መምበረ አግዘው እንዳሉት መንግስት ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የልማት ተግባራትን በማከናወን የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዚህም በአገሪቱ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ያለው የማይናወጥ አቋም የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተሳሳተ መንገድ ወደ ሰላም ያልመጡ ራሳቸውን ለውይይት ዝግጁ ማድረግ እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አለማየሁ ታዬ እንዳሉት ግጭት ያለንበትን ዘመን የማይመጥን፣ ዘርፈ ብዙ ጉዳት የሚያስከትል እንጂ ዘላቂ ሰላምና ልማትን የሚያረጋግጥ አይደለም ብለዋል፡፡ በመሆኑም በተሳሳተ ስሌት ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለምክክር መዘጋጀት እንዳለባቸው ሃሳባቸውን ሰጥተዋል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋሉ ግጭቶች በዘለቂነት ቢቋጩ የነዋሪውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆኑን አዲስ አበባ ምስክር ናት ያሉት አስተያየት ሰጪ ደግሞ ወይዘሮ ብርቄ ገብረ ዮሐንስ ናቸው፡፡ በመሆኑም ሁሉም ዜጋ ለሰላም በጋራ መስራት እንዳለበት ነው ያነሱት፡፡  
የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተደራሽነት ለማስፋት በቴክኖሎጂ የታገዘ ሥራ እየተከናወነ ነው
Jul 5, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦ሰባተኛውን ዙር ጠቅላላ ምርጫ ግልፅነትና ተደራሽነት ለማስፋት በቴክኖሎጂ የታገዘ ሥራ እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የሆኑ የዴሞክራሲ ተቋማት የሪፎርም ስራቸውን አስመልክቶ የጋራ የውይይት መድረክ እያካሄዱ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ የተቋማቸውን የሪፎርም ስራዎች አስመልክቶ ሪፖርት አቅርበዋል። በዚሁ ጊዜ ቦርዱ በህዝብና በመንግስት የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የነበሩበትን የአሰራር ክፍተቶች ለይቶ ለመፍትሄው ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል። በዚህም በህግና በአሰራር፣ በሰው ሃይልና አደረጃጀት ያሉ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ሪፎርም ማድረጉንም አመልክተዋል። ካለፉት ምርጫ ሂደቶች የተሻሉ ተሞክሮዎችን በመውሰድና ችግሮችን በመለየት ለቀጣዩ ምርጫ የበለጠ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ነው ያብራሩት። የሰባተኛውን ዙር ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒነት ያለው እንዲሆን በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ለመተግበር ዝግጅት እያደረገን ነው ብለዋል። በዚህም የምርጫ ሂደቱን ፈጣንና ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ የሞባይል መተግበሪያ በማበልፀግ የዕጩዎችንና የመራጮችን ምዝገባ በቴክኖሎጂ ለማከናወን ስራዎች ተጀምረዋል ነው ያሉት። ተቋሙ ነፃና ገለልተኛ ሆኖ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት በሰው ሃይልና በአደረጃጀት ራሱን ማብቃት የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የዕጩዎችና የመራጮችን ምዝገባ ለማካሄድ የሚያግዘው ቴክኖሎጂ አስተማማኝና በቦርዱ ባለሙያዎች የበለፀገ ሲስተም መሆኑንም ገልጸዋል። ምዝገባው በሞባይል መተግበሪያ፣ በቦርዱ ባለሙያዎች እገዛ እንዲሁም በማኑዋል መንገድ እንደሚከናወንም አመልክተዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችና መራጮች ስለ ቴክኖሎጂው አጠቃቀም በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እገዛ ይደረግላቸዋል ብለዋል። ለዚህ አሰራር የሚሆን አዋጅ ለምክር ቤቱ መቅረቡንም ነው ያመለከቱት። የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ዋና ዕምባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በበኩላቸው፤ ተቋሙ የተጣለበትን ኃላፊነት መወጣት የሚያስችለውን ሪፎርም ሲያከናውን ነበር ብለዋል። በዚህም አስተዳደራዊ በደሎችን መፍታት የሚያስችሉ የሰው ሃይልና አደረጃጀት መፍጠሩን በማንሳት።   በተያዘው በጀት ዓመት 11ወራት ከ2ሺ በላይ አቤቱታዎችን መርምሮ የውሳኔ ሀሳብ መስጠቱን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ፤ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ላይ የሚደርሱ ጥሰቶችን ማረም የሚያስችሉ ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት ተዘርግቶ ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል።   በተለይም የሰብዓዊ መብቶች ተጥሰዋል የሚሉ አቤቱታዎች ሲቀርቡ በሁለቱም ወገን ያለውን እውነታ በማጣራት ፍትሃዊና ትክክለኛ ሪፖርት እንዲወጣና ጥሰቱ እንዲታረም እየሰራ ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መተግበሩንም ጠቅሰው፤ የሰብዓዊ መብት አያያዝና አጠባበቅ የበለጠ እንዲጠናከር የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።  
መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ዘርፍ የተደራጀና ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ በአስተሳሰብና ሥነ-ልቦና የተገነባ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Jul 5, 2025 77
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ዘርፍ በወጉ የተደራጀ፣ ዘመኑን የዋጀ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ በአስተሳሰብና ሥነ-ልቦና የተገነባ ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ የ15ኛ ዙር መደበኛ ኮርስ ከፍተኛ መኮንኖችን አስመርቋል። በመርኃ ግብሩ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን እና የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሙሉጌታ አምባቸው፣ ጄኔራል መኮንኖች፣ ወታደራዊ አታሼዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።   የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኮሌጁ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም የመከላከያ ሠራዊት ክፍሎችና ኃይሎች ውስጥ በብቃት የመምራት ችሎታ ያላቸውን ከፍተኛ ታክቲካል የጦር ክፍሎችን፣ የኦፕሬሽናል ውጊያ ሳይንስና ጥበብ ሥልጠና የወሰዱ በርካታ ከፍተኛ መኮንኖች ማፍራቱን ተናግረዋል። በዚህ ዓመትም በኮሌጁ ስልጠና በመውሰድ በብቃት አጠናቀው ለምረቃ የበቁ ከፍተኛ መኮንኖች የመከላከያ ሠራዊት እያስመዘገበ ያለውን ብቁ የሰለጠነ ፕሮፌሽናል ሠራዊት የመገንባት ጥረት ውጤት መሆናቸውን ጠቅሰዋል። አገራዊ እና ተቋማዊ ሪፎርም ከተበሰረበት ጊዜ ጀምሮም ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገበች እንደምትገኝ ተናግረዋል። በመከላከያ ተቋማዊ ግንባታ መስክ ከፍተኛ ለውጥ እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው፤ ውጤቱ በቁርጠኛ የመንግስት አመራርና ፅናትን በተላበሱ የሠራዊት አዛዦችና በጀግናው ሠራዊታችን መስዋዕትነት ነው ብለዋል። የመከላከያ ሠራዊቱን ፕሮፌሽናል በማድረግና በማዘመን በቀጣይ ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶችን ከሩቅ የማስቀረት እንዲሁም ብሔራዊ አደጋ ቢከሰት በአስተማማኝ መቀልበስ የሚችል አቅም ያለው ሠራዊት ገንብተናል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ዘርፍ ተለውጦ በወጉ የተደራጀ፣ ዘመኑን የዋጀ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ በአስተሳሰብና ሥነ-ልቦና የተገነባ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም የወታደራዊ ስትራቴጂ ኦፕሬሽን፣ ስልታዊ ጥበብና እውቀትን የተላበሰና ኢትዮጵያን የሚመጥን የአገር መከላከያ ለመገንባት የተቀመጠውን ስትራቴጂ ለማሳካት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።   ተመራቂ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችም በመከላከያ አዛዥና ስታፍ ኮሌጅ በነበራቸው ቆይታ ያገኙትን ትምህርት፣ የተሟላ እውቀት፤ ክህሎትና አስተሳሰብ በመጠቀም ለዚህ አቅም መሆን አለባቸው ብለዋል። ተመራቂዎች በሚሰማሩባቸው የሠራዊቱ ክፍሎች የወታደራዊ ሥነ-ምግባር፣ የግዳጅ አፈፃፀም ብቃትና የማይናወጥ ሥነ-ልቦና ተምሳሌትና አርዓያ በመሆን እንዲያገለግሉ አስገንዝበዋል። ኮሌጁ የኢትዮጵያን መከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች ከማብቃት ባሻገር ከወዳጅ አገራት የመጡ ከፍተኛ መኮንኖችን ተቀብሎ በማስተማርና በማሰልጠን ወታደራዊ ትብብርና ዲፕሎማሲ ይበልጥ እንዲጠናከር በማድረግ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል ፡፡   በዛሬው ዕለትም ከበርካታ ወዳጅ አገሮች የመጡ ከፍተኛ መኮንኖች በኮሌጁ ሲሰጥ የቆየውን ትምህርት አጠናቀው ለምረቃ መብቃታቸውን አንስተዋል። ተመራቂ የወዳጅ አገሮች ከፍተኛ መኮንኖች በነበራችው ቆይታ ያገኙትን አቅምና ዕውቀት ለአገራቸው ተልዕኮ እንዲጠቀሙበት ያስገነዘቡት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ፤ ስልጠና የሰጠቻቸውን ኢትዮጵያ ከአገራቸው ጋር ለጠበቀ ወዳጅነት መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ይህ የትምህርትና ስልጠና ትብብርም በአገሮች መካከል ሊኖር የሚችልን ወታደራዊ ዲፕሎማሲ ወደ ከፍተኛ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ጠቅሰው ይህንንም አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
የኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመደራደር አቅም እየጎለበተ መጥቷል - የምክር ቤት አባላት
Jul 5, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመደራደር አቅም በተጨባጭ አየጎለበተ መምጣቱን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2017 በጀት ዓመት የመንግስትን የሥራ አፈጻጸምን አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወሳል። በዚሁ ወቅት ባለፉት ሰባት ዓመታት አገሪቷ ምንም ዓይነት ኮሜርሺያል (ከፍተኛ ወለድ ያለው) ብድር አለመውሰዷን ነው የገለጹት። ይሁን እንጂ ባለፉት መንግስታት የተከማቸ የውጭ ዕዳ ለመክፈል ከፍተኛ ጥረት ስታደርግና የብድር መክፈያ ጊዜውን ለማራዘም ስትደራደር መቆየቷን አብራርተዋል። በዚህም ባለፉት አራት ዓመታት ከተለያዩ መንግስታት ጋር በተደረገ ድርድር የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ ሽግሽግ መደረጉንም ነው ያነሱት። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል ነው ብለዋል። ብድር ለታለመለት ዓላማ ካልዋለ ለትውልድ ዕዳ መሆኑ እንደማይቀር ጠቁመው፤ መንግስት ይህን ዕዳ ለማቃለል እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎችንም አድንቀዋል። ረዳት ፕሮፌሰር ገነነ ገደቦ መንግስት ከተለያዩ አገራት የሚወስዳቸው ብድሮች ለታለመላቸው ዓላማ ማዋልና ብድሩን በጊዜ መመለስ ይገባል ይላሉ።   በከፍተኛ ወለድ የመጡ ብድሮች አገርና ትውልድ ላይ ጫና የሚፈጥሩና ተጨማሪ ልማት እንዳይኖር የሚያደርጉ በመሆኑ መንግስት በድርድር ዕዳውን ማሸጋሸጉ ተገቢ መሆኑንም አንስተዋል። ሌላዋ የምክር ቤት አባል ነጃት ግርማ (ዶ/ር)፤ ቀደም ሲል አገሪቷን ሲመሩ የነበሩ መንግስታት ለትውልዱ ከፍተኛ ዕዳ አሸጋግረዋል ነው ያሉት። ከለውጡ ዓመታት በኋላ መንግስት ይህን የትውልድ ዕዳ ለማቃለል እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎችንም አድንቀዋል።   የተለያዩ መንግስታት የኢትዮጵያን ዕዳ ለማሸጋሸግ ያሳዩት ፍላጎትም አገሪቷ በራሷ ለመልማት ያላትን አቋም ከማየት የመነጨ መሆኑን በማንሳት። ሌላው የምክር ቤት አባል ፈትህ መህዲ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት ምንም ዓይነት ከፍተኛ ወለድ ያለው ኮሜርሺያል ብድር አለመውሰዷ ዕዳዋን የመቀነስ ፍላጎቷን ያሳያል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፤ አገሪቷ ቀደም ሲል የወሰደቻቸው ብድሮች የእፎይታ ጊዜ ለማግኘት የተደረገው ሽግሽግ የአገሪቷን የመደራደር አቅም መጎልበት ያሳያል።   የምክር ቤቱ አባል ሰሚራ የሱፍም በዚህ ሀሳብ ይስማማሉ። የዕዳ ሽግሽጉም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያ ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነት መጠናከር የሚያሳይ ነው ብለዋል። ምክር ቤቱ የሚቀርቡለት የብድር ስምምነቶች ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ በአግባቡ በመፈተሽ እንደሚያጸድቅም ነው አባላቱ የገለጹት።
ማህበራዊ
መገናኛ ብዙሃን ፍጥነትና ፈጠራ የታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ላይ አተኩረው ሊሰሩ ይገባል -አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ
Jul 5, 2025 58
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦የድህረ-እውነት ዘመን ተግዳሮቶችን ለመሻገር መገናኛ ብዙሃን ፍጥነትና ፈጠራ የታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ላይ አተኩረው ሊሰሩ እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ አስገነዘቡ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የዴሞክራሲ ተቋማት የሪፎርም ሥራቸውን በተመለከተ የጋራ ምክክር መድረክ አካሂደዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ በሚያደርግላቸው መገናኛ ብዙሃን ያሉ ችግሮችን በመጋፈጥ የተሻለ የይዘት ስራ እየሰሩ ናቸው። በመድረኩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የሥራ ሃላፊዎች የሪፎርም ሥራዎችን አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ተቋማዊ ሪፎርም አስመልክቶ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሠይፈ ደርቤ ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት፤ ኢዜአ ብሄራዊ ጥቅምን የማስጠበቅና ብሄራዊ መግባባትን የመፍጠር ተልዕኮውን በአግባቡ ለመወጣት የተለያዩ ተግባራትን አከናውኗል። የኢዜአ ማቋቋሚያ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ በሰው ሃይል፣ በአሰራርና አደረጃጀት ለይቶ ወደ ሥራ መግባቱንም አስታውሰዋል። ኢዜአ በአገር ውስጥና በውጭ ቋንቋዎች የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁና የአገር ገፅታ የሚገነቡ ጠንካራ የይዘት ስራዎችን እያሰራጨ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ተቋሙ በዲጂታል ሚዲያውም የኢትዮጵያን እውነትና መሻት የሚያንፀባርቁ ይዘቶችን ለአገር ውስጥና ለውጭ መገናኛ ብዙሃን ተደራሽ እያደረገ ነው ብለዋል። በአሁን ወቅትም በአምስት የአገር ውስጥና በሶስት የውጭ ቋንቋዎች የኢትዮጵያን ፍላጎት የሚያሳዩና ገፅታ የሚገነቡ መረጃዎችን ተደራሽ እየተደረገ ነው ብለዋል። ኢዜአ የተሰጠውን አገራዊ ተልዕኮ መወጣት የሚያስችለውን የህግና አሰራር ክፍተቶች ከመሙላት አኳያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላደረገውና እያደረገ ስላለው ድጋፍም አመስግነዋል። የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው፤ ኢቢሲ ችግሮችን በጥልቅ በመለየት ከአገራዊ ለውጡ በኋላ የይዘት፣ የገበያ፣ የቴክኖሎጂና የኮርፖሬት ሪፎርሞችን በማካሄድ ወደ ሥራ መግባቱን ተናግረዋል። በዚህም የፈጠራ ዘርፍ በማቋቋምና በክልል ያሉ ሃብቶችን ጥቅም ላይ ለማዋል የጀመራቸው ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን ነው የተናገሩት። ኢቢሲ ባሉት የቴሌቪዥን፣ የሬድዮና የዲጂታል አማራጮች ገዥ ትርክትን የሚያሰርፁ ጠንካራ የይዘት ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ መሳፍንት ተፈራ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ሚዲያው መስፋፋትን ተከትሎ በህትመት ውጤቶች ላይ የተጋረጡ ፈተናዎችን ለመሻገር የተለያዩ ሪፎርሞች መደረጋቸውን ነው ያብራሩት። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንደገለጹት፤ በድህረ እውነት ዘመን የሀሰተኛ እና የጥላቻ ንግግር ላይ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በዕውቀትና እውነት ላይ ተመስርቶ የሚሰራ መገናኛ ብዙሃን ያስፈልጋል። ምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ በሚያደርግላቸው መገናኛ ብዙሃን ያሉ ችግሮችን በመጋፈጥ የተሻለ የይዘት ስራ ለመስራት እያደረጉት ያሉውን ጥረት ያደነቁት አፈ ጉባዔው፤ የድህረ-እውነት ዘመን ተግዳሮቶችን ለመሻገር መገናኛ ብዙሃኑ ፍጥነትና ፈጠራ ለታከለባቸው የይዘት ሥራዎች ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል። ምክር ቤቱም ለዴሞክራሲ ተቋማቱ ውጤታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው የገለጹት። የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ በበኩላቸው፤ ከአገራዊ ለውጡ በኋላ መገናኛ ብዙሃን ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያለውን ቁልፍ ሚና በመረዳት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። በድህረ እውነት ዘመን የመገናኛ ብዙሃን ገዥ ትርክትን ለማስረፅ የጀመሩትን ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። ኢዜአ ከተመሰረተ ረጅም ዓመታት ቢያስቆጥርም በየጊዜው የሚያጋጥሙትን ፈተናዎች እየተሻገረ አሁን የደረሰበት ደረጃ በመድረሱ አድንቀዋል። በምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በመገናኛ ብዙሃን ላይ የነበሩ የአሰራርና አደረጃጀት ችግሮች በሂደት እየተፈቱ መምጣታቸውን ነው ያነሱት። ኢዜአ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፎ አስተማማኝ የዜና ምንጭ ለመሆን እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑንም ተናግረዋል።
በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት 63 ሚሊዮን ዜጎች ተጠቃሚ ሆነዋል
Jul 5, 2025 51
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በ2017 በጀት ዓመት የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ ዜጎች ቁጥር 63 ሚሊዮን መድረሱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የምግብና ሥርዓት ምግብ እንዲሁም የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚሁ ወቅት፥ ስርዓተ ምግብን ማሻሻል ጤናማና አምራች ትውልድ ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የምግብና ስርዓተ ምግብ የ10 ዓመት ስትራቴጂና የሰቆጣ ቃልኪዳን ማስፋፊያ ምዕራፍ ባለፉት አራት ዓመታት ተስፋ ሰጪ በሆነ መንገድ እየተተገበሩ መሆኑን አንስተዋል። በሰቆጣ ቃልኪዳን በማስፋፋት ምዕራፍ ትግበራው በ2017 በጀት ዓመት በ334 ወረዳዎች መተግበሩን ተናግረዋል። በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሚያጠቡና ነፍሰጡር እናቶች እንዲሁም ህጻናት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሰቆጣ ቃል ኪዳን አበርክቶን ለማሳደግ በ2018 ዓ.ም የሚተገበርባቸውን ወረዳዎች 520 ለማድረስ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። በቃልኪዳኑ መሠረት በ2022 ዓ.ም መቀንጨርን ዜሮ ለማድረግ የምግብና ስርዓተ ምግብ ተግባራትን ሽፋን ማሳደግ እንዲሁም በቂ ሀብት መመደብ ላይ በሁሉም ክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ተመሳሳይ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባው አንስተዋል። ሥርዓተ ምግብን ለማሻሻልና ሀገራዊ የጤና ግቦችን ለማሳካት የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሻራ እና ሌሎች ኢኒሼቲቮች ወሳኝ ሚና እያበረከቱ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሁሉን አቀፍ የጤና ተደራሽነትን እውን ለማድረግ የማይበገር የጤና ስርዓት በመገንባትና የጤና መሰረተ ልማትን በማስፋት የጤና አገልግሎት ሽፋንን ከ95 በመቶ በላይ ማድረስ ተችሏል ነው ያሉት። የጤና መድህን ስትራቴጂ መክፈል የማይችሉ ዜጎችን የጤና ዋስትና ለማሳደግ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት እየተተገበረ መሆኑን ገልጸዋል። የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ሽፋን በ2017 በጀት ዓመት ወደ 1ሺህ 195 ወረዳዎች ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል። በዚህም 63 ሚሊዮን ዜጎች በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን መርሃግብር ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ አንስተዋል። ይህም የተሳካው በሁሉም ክልሎች የመክፈል አቅምን መሰረት ያደረገ አሰራር በመተግበሩ ነው ብለዋል።
በስርዓተ ምግብ፣ በሰቆጣ ቃልኪዳንና የማህበረሰብ ጤና መድህን አገልግሎት ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jul 5, 2025 41
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦በስርዓተ ምግብ፣ በሰቆጣ ቃልኪዳንና የማህበረሰብ ጤና መድህን አገልግሎት ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። መርሃ-ግብሮቹ የአመራሩ ቁርጠኝነትና የማህበረሰቡ የባለቤትነት ተሳትፎ ስኬት ማሳያዎች እንዲሁም ለሌሎች ፕሮግራሞች ትግበራ ልምድ የሚወሰድባቸው ሀገር በቀል መፍትሔዎች መሆናቸውንም ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የምግብና ሥርዓት ምግብ እንዲሁም የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ ነው።   መቀንጨርንና ሌሎች የስርዓተ-ምግብ ችግሮችን ለመቅረፍ ማሕበረሰቡን ማዕከል ያደረጉ ተግባራትን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በምግብ እና ስርዓተ ምግብ ስትራቴጂ እና በሰቆጣ ቃል ኪዳን የተቀመጡ ግቦች ሊሳኩ የሚችሉት የማሕበረሰብ ንቅናቄ በመፍጠር የችግሩ መፍትሔ ሰጪ በማድረግ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ አንጻር በሰቆጣ ቃል ኪዳን የማስፋፋት ምዕራፍ ትግበራ ህዝቡን ባለቤት በማድረግ፣ ሀብትና ጉልበትን በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። የስርዓተ ምግብ ችግሮችን በመለየት በራስ አቅም መፍታት የሚያስችሉ አካባቢያዊ ፈጠራዎችን በወረዳዎች እና ቀበሌዎች መተግበር መቻሉ እየመጣ ላለው ለውጥ ቁልፍ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል፡፡   የሰቆጣ ቃል ኪዳን ትግበራ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ጠቅሰው፥ የማስፋፋት ምዕራፍ በመጪው ዓመት እንደሚጠናቀቅም ገልጸዋል። በ15 ዓመታት ፍኖተካርታው መሠረትም ወደ ቀጣዩ የ5 ዓመታት የማስፋት ምዕራፍ ሽግግር ቁልፍ ተግባራትን ማከናወን ይገባል ነው ያሉት፡፡ በቤተሰብ ደረጃም ለውጥ ማምጣት የሚያስችሉ አካሔዶችን መለየትና ውጤት ሊያመጡ የቻሉና አዋጪ ፈጠራዎችን ማስፋፋት እንደሚገባ አስረድተዋል። በጤናው ዘርፍም የጥራት ደረጃውን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለሁሉም ዜጎች በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ ሁሉን አቀፍ የጤና ሽፋን ግብን ለማሳካት የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድኅን ፕሮግራም እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል። በ2017 በጀት ዓመት የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድኅን ትግበራ በርካታ ዜጎች የጤና መድኅን ሽፋን ማግኘታቸውንም አንስተዋል።   የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድኅን ፕሮግራም የህክምና ወጪ ስጋትን በመቅረፍ የዜጎችን የኑሮና የጤና ሁኔታ በማሻሻል ቁልፍ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። ከምግብ እና ስርዓተ ምግብ ስትራቴጂ እንዲሁም የሰቆጣ ቃል ኪዳን ትግበራን ለማፋጠን በቀጣይም ተቋማዊና ማህበረሰባዊ ተግባራትን ማሳለጥ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የዲጂታል አሰራር በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ ነው
Jul 5, 2025 76
አዳማ ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የዲጂታል አሰራር በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ ተናገሩ። የባለስልጣኑ የስራ ሃላፊዎች የአገልግሎቱን የአዳማ እና አዲስ አበባ የህክምና መሳሪያዎች እንዲሁም መድሀኒቶች አያያዝና አጠቃቀም ያለበትን ሁኔታ ጎብኝተዋል።   ከጉብኝቱ በኋላ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡት የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ መሰረት መስቀሌ፤ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈው የአገልግሎቱ የመድሀኒትና የህክምና መሳሪያዎች አያያዝ፣ አጠቃቀምና አወጋገድ በጥሩ ምሳሌነት የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል።   የአገልግሎቱን የቅርንጫፍ መጋዘኖችን ከዋና መስሪያ ቤቱ መጋዘን ጋር በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማገናኘት ቁጥጥርና አሰራሩን ቀልጣፋ ማድረግ መቻሉንም አድንቀው የመድኃኒት ብልሽት፣ ብክነት፣ ሌብነትና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል። የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው መድ`ሃኒቶችና የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶችም በአግባቡ ተለይተው እየተቀመጡና አስተማማኝ በሆነ መልኩ እየተወገዱ መሆኑን አረጋግጠናል ብለዋል። የማቀዝቀዣ ማሽኖች በመጋዘኖች አግባብ የሆነ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም በጉብኝታችን አይተናል ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ የሚወገዱ መድኃኒቶችና የህክምና ቁሳቁሶች እንዲሁም ኬሚካሎች የሚወገዱበት የአዳማ ማዕከል ደረጃውን የጠበቀ መሆኑንም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በአገልግሎቱ 19 ቅርንጫፎች እና 63 መጋዝኖች የዲጂታል አሰራር ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል።   ከግዥና ስርጭት በተለይም ከተገዙበት አገር ጀምሮ እስከ ክምችት እንዲሁም የስርጭት ሰንሰለቱን በተመለከተ በቀላሉ መከታተልና መቆጣጠር የሚያስችል አሰራር ተግባራዊ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም ዓለም አቀፍ የማከማቻ መጋዘኖችን ደረጃ የጠበቀ የማስፋፊያ ስራ የማከናወን እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ኢኮኖሚ
የገጠር መሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሬታችንን ለማልማት ይገጥመን የነበረን የፋይናንስ ብድር ችግር ፈቶልናል- አርሶ አደሮች
Jul 5, 2025 54
ወላይታ ሶዶ፣ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦የገጠር መሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ማግኘታቸው መሬታቸውን ለማልማት ይገጥማቸው የነበረን የፋይናንስ ብድር ችግር ለመፍታት ማስቻሉን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች ገለጹ። በክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ኤጀንሲ ''መሬት የሀብት ሁሉ ምንጭ ነው'' በሚል መሪ ሀሳብ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ያዘጋጀው ኮንፍረንስ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።   ኢዜአ ካነጋገራቸው የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች መካከል የጌዴኦ ዞን አርሶ አደር አስማማው እንዳሉት የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ማግኘታቸው መሬታቸውን በአግባቡ አልምተው ተጠቃሚነታቸውን ለመሳደግ አግዟቸዋል። በተለይ ከዚህ ቀደም የቡና ልማት ሥራቸውን ለማስፋፋት ይገጥማቸው የነበረን የገንዘብ ችግር እንደፈታላቸው ነው የገለጹት።   ከወላይታ ዞን የመጡት አርሶ አደር ተስፋዬ ቱካ በበኩላቸው የይዞታ ማረጋገጫው ከዚህ ቀደም ከእርሻ መሬት ወሰን ጋር በተያያዘ ይገጥማቸው የነበረን ውዝግብ ለመፍታት እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። የመሬት ልኬት ምስክር ወረቀት ካገኙ ወዲህ በወሰዱት ብድር የግብርና ሥራቸውን በማስፋፋት ከራሳቸው ባለፈ ለ12 ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል።   የመሬት አስተዳደር ሥርዓቱን በማዘመን የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰራው ሥራ 386 ሺህ አርሶ አደሮችን ወደ ቋት ማስገባት ተችሏል ያሉት ደግሞ የወላይታ ዞን መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አስፋው ሴታ ናቸው።   አርሶ አደሮች የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተራቸውን ዋስትና በማስያዝ ከብድር አቅራቢ ተቋማት ገንዘብ በመበደር የግብርና ልማት ሥራቸውን እያስፋፉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በክልሉ ግብርና ቢሮ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ኤጄንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኖህ ታደለ በበኩላቸው የገጠር መሬት አያያዝና አጠቃቀምን ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ ህገወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል፣ የመሬት አስተዳደር ሥርዓቱን ለማዘመንና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ማገዙን ጠቁመዋል።   በክልሉ የ2ኛ ደረጃ መሬት ልኬት በተካሄደባቸው 48 ወረዳዎች ከ2 ሚሊዮን 48 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች የገጠር መሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር አግኝተዋል። ተግባሩን በማጠናከር በቀጣይም በ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ማሳዎች ላይ ልኬትና ምዝገባ ለማካሄድ መታቀዱን ጠቁመዋል። አርሶ አደሮች የማረጋገጫ ደብተሩን በመጠቀም ከፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ መበደር እንዲችሉ በመደረጉ የበርካቶች ኑሮ እየተሻሻለ መምጣቱንም ዋና ሥራ አስኪያጁ አክለዋል። በመድረኩ የክልሉ መንግስት የሥራ ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።  
በጎንደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማውን እድገት የሚያፋጥኑ ናቸው
Jul 5, 2025 55
ጎንደር፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፡- በጎንደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማውን እድገት የሚያፋጥኑና የህዝቡንም የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸው ተገለጸ። የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ፣ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ የስራ ሃላፊዎች በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ዋና አፈጉባኤዋ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በጉብኝቱ ላይ እንደተናገሩት፤ በከተማው የሚካሄዱ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተቀናጅቶ የመምራትና ጀምሮም የማጠናቀቅ ተቋማዊ አቅምና የአመራር ቁርጠኝነት የታየበት ነው።   በተለይ የከተማው የኮሪደር ልማት ስራ ሕዝቡን በባለቤትነት በማሳተፍ በአጭር ጊዜ ውስጥ የታየው ለውጥና የተመዘገበው ስኬት በሞዴልነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። የኮሪደር ልማት ስራው የከተማውን ውበት የገለጠ ምቹና ውብ የከተሜነት ገጽታን ያላበሰና ለዜጎችም የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።   በተጨማሪም በከተማው እየተካሄደ ያለው የሴፍቲኔት መርሀ ግብር በከተሞች የሚታየውን ድህነት በመቀነስ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች ጥሪት አፍርተው በአጭር ጊዜ ከድህነት የሚወጡበት ምቹ የኢኮኖሚ መደላድል የፈጠረ እንደሆነ መገንዘባቸውን ተናግረዋል።   በከተማው እየተገነባ ያለው ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ከህገ ወጥ ደላሎች ነጻ በሆነ መንገድ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ገበያውን በማረጋጋትና የኑሮ ውድነቱን በመቀነስ በኩል የጎላ ፋይዳ እንዳለውም ገልጸዋል። የጠራ እቅድና ሀሳብን ወደ ተግባር ለመለወጥ የአመራሩና የሕብረተሰቡ የተቀናጀ እንቅስቃሴና ጥረት የሚበረታታ መሆኑን አስረድተዋል። የክልሉ ምክር ቤት ሴቶች ህጻናት ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ አበራሽ ታደሰ በበኩላቸው፤ በከተማው እየተካሄደ የሚገኘው የሴፍቲኔት መርሀግብር የሴቶችን ኑሮና የስራ ባህል የቀየረ የገንዘብ ቁጠባ ባህላቸውንም ያሳደገ ነው ብለዋል።   በከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ለቴክኖሎጂ መስፋፋትና ለወጣቶች የስራ እድል ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሱሌይማን እሸቱ ናቸው። የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ፤ የተካሄደው ጉብኝት የከተማ አስተዳደሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት እንዲያከናውን በቂ ግብአት የተገኘበት ነው ብለዋል።   በጉብኝቱ የኮሪደር ልማት ስራን ጨምሮ ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ግንባታ፣ የከተማ ሴፍቲኔት ስራዎች ፣ የአረጋውያን የምገባ ማዕከልና የአረንጓዴ አሻራ ዝግጅት ምልከታ የተካሄደ ሲሆን፤ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በጎሃ ተራራ ላይ ተከናውኗል።  
በኦሮሚያ ክልል ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በርካታ ባለሃብቶች በኢንቨስትመንት ዘርፍ እየተሳተፉ ይገኛሉ
Jul 5, 2025 65
ክልል፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች በኢንቨስትመንት ዘርፍ በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ተገለጸ። የሸገር አለም አቀፍ የኢንቨስትመንት አውደ ርዕይና ባዛር ዛሬ በአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር ተከፍቷል።   ለሶስት ቀናት የሚቆየው አውደ ርዕዩ የሸገር ከተማን የኢንቨስትመንት አማራጮች ይበልጥ በማስተዋወቅ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶችን ለመሳብ ትልቅ ሚና እንዳለው የከተማ አስተዳደሩ ገልጿል ።   በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባዔ ሳአዳ አብዱራህማን እና በኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎችም የፌደራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። በዚህ ወቅት የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሳአዳ አብዱራህማን ባደረጉት ንግግር፤ የክልሉ መንግስት የኢንቨስትመንት አስተዳደርን በማሻሻል የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶችን በስፋት ለማሳተፍ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ባደረጉት ክትትል ማረጋገጣቸውን ገልጸዋል።   በክልሉ ያለውን ምቹ መደላድል በመጠቀምም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች በኢንቨስትመንት ዘርፉ በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በኢንቨስትመንት ዘርፉ የስራ እድል ለመፍጠር፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመተካት፣ የወጭ ንግድ ለማሳደግ ብሎም ጥራት ያለውና ተወዳዳሪ ምርቶችን ለማምረት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የክልሉ መንግስት በተለይ ሸገር ከተማ ያላትን መልካ ምድር እና ለባለሃብቶች በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጠቅሞ የኢኮኖሚ ማዕከል እንድትሆን ያከናወነው ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። በሸገር ከተማ አዘጋጅነት ዛሬ የተከፈተው አለም አቀፍ የኢንቨስትመንት አውደ ርዕይ ከተማው ለኢንቨስትመንት ያለውን ምቹ ሁኔታ ማስተዋወቅ፣ ልምድ ልውውጥና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። በኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የሸገር ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሸገርን የኢኮኖሚ ማዕከል የማድረግ ራዕይን እውን ለማድረግ የኢንቨስትመንት ስራን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን በተከናወነው ስራም በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።   የተዘጋጀው የሸገር አለም አቀፍ የኢንቨስትመንት አውደ ርዕይ በከተማው ያለውን የኢንቨስትመንት ስራ እንቅስቃሴ እና አካባቢው ለኢንቨስትመንት ያለውን ምቹ ሁኔታ ለማስተዋወቅ እንደሆነ ተናግረዋል። በአውደ ርዕዩ ላይ በርካታ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሀብቶች ምርትና አገልግሎታቸውን ማቅረባቸውን ያወሱት ከንቲባው፤ ይህም ልምድ ለመለዋወጥ ምቹ መሆኑን ገልጸዋል። ዝግጅቱ ለቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የከተማ ገቢን ለማሳደግና የስራ እድል ለመፍጠር የበኩሉን አስተዋፅኦ እንደሚያበረክትም ጠቁመዋል። የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ሸገር ከተማ ለዘርፉ ልማት ያለውን ምቹ ሁኔታ እንዲጠቀሙ ከንቲባው ጥሪ አቅርበዋል። የአውደ ርዕዩ ተካፋይ ባለሀብቶችም ፤ በዝግጅቱ በመሳተፋቸው ከሌሎች ባለሀብቶች ጋር የልምድ ልውውጥ ለማድረግ፣ የገበያ ትስስር ለመፍጠርና ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅ እድል እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።  
በመዲናዋ ተገንብተዉ የተጠናቀቁ ከ15 ሺህ 960 በላይ ፕሮጀክቶች ከነገዉ ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናሉ
Jul 5, 2025 57
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በመዲናዋ ተገንብተዉ የተጠናቀቁ ከ15 ሺህ 960 በላይ ፕሮጀክቶች ተመርቀዉ ከነገዉ እለት ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ገለፁ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እናትዓለም መለሰ፤በ2017 በጀት ዓመት በመዲናዋ የተገነቡ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በዚህም ከተማ አስተዳደሩ በ2017 በጀት ዓመት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው የጎላ ዘርፈ-ብዙ የልማት ስራዎችን በማቀድና ተግባራዊ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ ለአገልግሎት ክፍት ከሚሆኑት እና ከሚመረቁትፕሮጀክቶች መካከል የመንገድ፣ የውሃ፣ የቤቶች ልማት ፣ የመስሪያ ቦታዎች፣ የወጣቶች ስፖርት ማዘወተሪያ ሜዳዎች፣ በአረንጓረዴ ልማት የተሰሩ እና ሌሎች ለህብረተሰቡ ፋዳቸው ጉልህ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ያካተቱ ናቸው ተብሏል፡፡ ፕሮጀክቶቹ በ91 ቢሊዮን ብር ወጪ በመንግስት እና በ4 ቢሊየን ብር ወጪ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡ ሲሆን፤የተጠቀሰው በጀት ብቻ ሳይሆን ሌሎች በሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችም በፈጣን ክትትል ሥራው ውስጥ እንዳሉ ወ/ሮ እናት ዓለም መለሰ በሰጡት ማብራሪያ ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ አጠቃላይ ከተያዘለት በጀት ውስጥ 71 በመቶ የሚሆነዉን ለካፒታል ፕሮጀክት ግንባታ እና ለድህነት ቅነሳ ፕሮግራም እንዲውል በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም ለትራንስፖርት ለዳቦ ፋብሪካ ድጎማ፣ለባሶች ግዥ፣ለተማሪዎች ምገባ፣ ለጤና መድህን ፕሮግራሞች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም የቢሮ ኃላፊዋ አስረድተዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ለወጣቶች ስራ እድል በሰጠዉ ትኩረት ከ366ሺ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸውም ተናግረዋል፡፡
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ብልጽግናን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ከጠባቂነት የተላቀቀ አስተሳሰብ መገንባት ቁልፍ ጉዳይ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 5, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦ብልጽግናን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ከጠባቂነት የተላቀቀ አስተሳሰብ መገንባት ቁልፍ ጉዳይ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው "የሚሰሩ እጆች ወግ" የተሰኘ ፕሮግራም በይፋ አስጀምሯል ። በመርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር፣ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የቦርድ ሰብሳቢና የብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ፣ የሃይማኖት አባቶች፡ የአገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች፣ ስራ ፈጣሪዎች፣ ወጣቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ፕሮግራሙ በየ15 ቀኑ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የሚቀርብ ሲሆን በስራ ፈጠራ ረገድ ትውልድን የሚቀርጹ ሃሳቦችን የሚያንሸራሽሩበት መሆኑ ተመልክቷል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት ከተረጅነት በመላቀቅ ወደ ብልጽግና የሚያደርሱ ትልሞችን ይዘን እየሰራን ነው ብለዋል። የተያዘው ትልም የሚሳካው ጠንክረን ስንሰራ ብቻ ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች ለዚህም ሰርተው የተለወጡ አገራት አብነት ሊሆኑን ይገባል ነው ያሉት። ከስራ ማማረጥና ስንፍና መላቀቅ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ማህበረሰቡ ውስጥ ግንዛቤን የማስፋቱ ጉዳይ አጽንኦት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። በመሆኑም የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎችን ጨምሮ ትውልድን የሚያንጹ ተቋማት የዜጎችን የስራ ባህል ለመቀየር የሚያስችሉ ግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን አበክረው ሊሰሩ እንደሚገባ አመልክተዋል። በትምህርት ተቋማትና በስራ ቦታዎችም ዜጎችን የማንቃት ስራ ሊጠናከር ይገባል ብለዋል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው፤ የስራ ባህልን ለማሳደግ እንደሀገር የማህበረሰብ ምርታማነት ምክክር መርሃ ግብር ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል ። የምክክር መርሃ ግብሩ ማህበረሰቡ በየአካባቢው ያለውን ጸጋ በማየትና በመስራት ውጤታማ እንዲሆን በር የሚከፍት መሆኑን ጠቅሰዋል ። ፕሮግራሙ ለስራ ባህል ማደግ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ትልቅ እርምጃ መሆኑንም ተናግረዋል።   ዘመኑ የሚጠይቀው አርበኝነት ሰርቶ በመለወጥ ራስን መቻል ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ የሚሰሩ እጆች ግለሰብንም አገርንም የሚያሳድጉ መንገዶች ናቸው ብለዋል ። በትኩረት ከተያዘ የስራ ባህል ላይ ተጨባጭ ውጤት እንደሚመጣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ማሳያ መሆኑንም አንስተዋል። አገርን ለማሻገር ስራን የማሰቢያ መንገድ፤ ትጋትና ታታሪነትን መርህ በማድረግ ልንረባረብ ይገባል ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ለ366ሺህ ስራ ፈላጊዎች ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል ። የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበት ስርአት መዘርጋቱንም ጠቁመዋል።
የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማስቀጠል የምርምር ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ-የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዮት
Jul 4, 2025 87
አዲስ አበባ፤ሰኔ 27/2017(ኢዜአ)፦የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማስቀጠል የተጀመሩ የምርምር ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዮት ገለፀ። ኢንስቲትዮቱ በቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ የ2017 አረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል። በቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል የተለቀቁ ቴክኖሎጂዎችን የሚያሳይ ኤግዚቢሽንም ከፍቷል።   የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሳ (ፕ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን እየሰራ ነው። የተሻሻሉ ዝርያዎችን በማውጣት የማባዛትና ለአርሶ አደሩ ተደራሽ የማድረግ፣ በአስተራረስና አመራረት ሂደት ዘዴዎች ላይ ክህሎት የማሳደግ ስራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ኢንስቲትዩቱ ባሉት 23 ማዕከላት የተለያዩ የምርምር ስራዎችን በማከናወን ዘርፉን የመደገፍ ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤በቀጣይም የግብርናውን እድገት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል። በኤግዚቢሽኑ የቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከልም የተለያዩ ምርምሮችን በማካሄድ የሰብልና እንስሳት ዝርያዎችን የማባዛትና ተደራሽ የማድረግ ስራ እያከናወነ መሆኑን መመልከታቸውን ገልፀዋል። ኢንስቲትዩቱ ዛሬ በቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ማስጀመሩን አንስተው፤ በ23ቱም ማዕከላት መርሃግብሩ እንደሚከናወን ጠቁመዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን በመትከል የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ብለዋል።   የቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ዳኜ ሞጆ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ከ70 ዓመት በላይ በተለያዩ ሰብልና እንስሳት ላይ ምርምር በማድረግ ዝርያዎችን ሲያሻሽል መቆየቱን ገልጸዋል። ያከናወናቸው ተግባራት ለግብርናው ዘርፍ እድገት አስተዋፅኦ ያላቸው እንደሆኑም ተናግረዋል። በማዕከሉ በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉት የአቮካዶና ፓፓዬ የቡናና ወይራ ችግኞች መሆናቸውን ተናግረዋል። የማዕከሉ የጤና ስፖርት ማህበር ሊቀ መንበር ግዛቸው ካባ እና የሰው ሀብት ክፍል ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ ድንቅነሽ አየለ፤ ዕጽዋቱ የአካባቢ ስነ ምህዳርን ለመጠበቅ የሚረዱ መሆናቸውን ጠቁመው፤ችግኞችን ከመትከል ባለፈ በመንከባከብ ለፅድቀት ለማድረስ የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
የተቀናጀ የአረምና የተባይ መከላከል ዘዴን ለማስፋፋት እየተሠራ ነው-ግብርና ሚኒስቴር
Jul 4, 2025 69
አርባምንጭ ፤ሰኔ 27/2017 (ኢዜአ)፡- በሀገሪቱ የተቀናጀ የአረምና የተባይ መከላከል ዘዴን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በተቀናጀ የአረምና የተባይ መከላከያ ዘዴ ዙሪያ በአርባ ምንጭ ከተማ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው። በመድረኩ ላይ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር) የግብርናው ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተቀናጀ የአረምና የተባይ መከላከያ ዘዴን ለማስፋፋት እየሠራ ይገኛል ብለዋል። ፓርቲኒየም ወይም የቅንጨ አረም በእርሻና በግጦሽ መሬት ላይ በመስፋፋት እንዲሁም ኋይት ስኬል (Mango White scale) የተሰኘው የማንጎ በሽታ በምርትና ምርታማነት ብሎም በእንስሳትና ሰዎች ጤና ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ መሆኑን ገልጸዋል።   አካባቢን ከሚበክል አሠራር በመውጣት አረምና ተባዮችን በተፈጥሯዊ ወይም ባዮሎጂካል መንገድ ለማስወገድ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በተለይ ድንበር ዘለል የሆኑ አንበጣ፣ ወፎችና ሌሎች ተባዮችን ለመከላከል የአሰሳና የኬሚካል ርጭት ሥራ የሚያከናውኑ አምስት አይሮፕላኖችን ተገዝተው ወደ ሥራ መገባቱን ጠቅሰዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ዓለም አቀፍ የስነ-ነፍሳትና ስነ-ምህዳር ምርምር ተቋም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአርባ ምንጭ ዕፅዋት ማዕከል የገነባውን ስነ-ህይወታዊ ፀረ-ተባይና ፀረ-አረም ላቦራቶሪ በዛሬው ዕለት መርቀው ከፍተዋል። ዓለም አቀፍ የስነ-ነፍሳትና ስነ-ምህዳር ምርምር ተቋም ተወካይና ተመራማሪ ሚናሌ ካሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋሙ የህብረተሰቡን የጤና፣ የሰብል፣ የስነ-ምህዳርና ሌሎች ችግሮችን በተቀናጀ መንገድ ለመፍታት ጥናትና ምርምር ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸዋል።   ፓርቲኒየም የተሰኘውን አረም ከሌሎች ከሚወገዱ ቁሶች ጋር በማደባለቅ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማምረት የሚያስችል ሥራ ከአርባ ምንጭ ዕፅዋት ማዕከል ጋር መስራቱን ተናግረዋል። በተጨማሪም የማንጎ በሽታን የሚከላከል ነፍሳት ማራቢያ ላቦራቶሪ ገንብተው ለዕፅዋት ማዕከሉ ማስረከባቸውን ገልጸዋል። በአርባ ምንጭ ዕፅዋት ማዕከል የተገነባው ተባይን በተባይ የመቆጣጠር ዘዴ እንዲሁም በፓርቲኒየም የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ዘዴ ለግብርና ምርታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው የጠቆሙት ደግሞ የማዕከሉ ኃላፊ አቶ ሙላለም መርሻ ናቸው።   ቴክኖሎጂው ህብረተሰቡን ከኬሚካል ጥገኝነት የሚያላቅቅ ከመሆኑም በላይ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ፣ ንጹህ አካባቢን ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚያግዝ ነው ብለዋል። ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው መድረክም ከኬኒያ የመጡ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጨምሮ የፌዴራል መንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ዓለም አቀፍ የስነ-ነፍሳትና ስነ-ምህዳር ምርምር ተቋም ተወካዮች፣ ተመራማሪዎች እና ማህበራት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።  
የኮደርስ ስልጠና የተሻለ የዲጂታል እውቀትና ክህሎት እንድናገኝ መልካም አካጣሚ ፈጥሮልናል - ወጣቶች
Jul 4, 2025 87
ጂግጂጋ፤ ሰኔ 27/2017(ኢዜአ)፦ የኮደርስ ስልጠና የተሻለ የዲጂታል እውቀትና ክህሎት እንድናገኝ መልካም አካጣሚ ፈጥሮልናል ሲሉ በጂግጂጋ ከተማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ወጣቶች ተናገሩ። የሶማሌ ክልል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ በበኩሉ በክረምቱ በእረፍት ላይ የሚገኙ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከወሰዱ ወጣቶች መካከል ሸርማርኬ ሸኪብ አብዲ፤ የስልጠናው እድል በተለይም ለወጣቶች ጥሩ አጋጣሚ በመሆኑ ጥሩ የዲጂታል እውቀት እና ክህሎት እንድንጨብጥ እያደረገን ነው ብሏል። ከስልጠናው በቀሰመው እውቀት እና ክህሎት በመታገዝ ዌብሳይት በማበልጸግ የራሱን የንግድ ስራ ለማስተዋወቅ እየተጠቀመበት መሆኑን አንስቶ በነፃ እንዲህ አይነት የትምህርት እድል በማግኘቱ አመስግኗል። የሚገኘው እውቀት ከሀገርም ባለፈ ዓለም አቀፍ ተፈላጊ የሚያደርግ መሆኑን አንስቶ ሌሎች ወጣቶችም እድሉ እንዳያመልጣቸው መክሯል። ሌሎች ስልጠናውን ያገኙት ወጣት አብዲሸኩር መሀመድ አብዲ እና ሰከሪዬ አብዲረህማን ዓሌ፤ የኮደርስ ስልጠናው በብዙ መልኩ ጠቃሚ መሆኑን ካገኘነው እውቀትና ክህሎት ተገንዝበናል ብለዋል። የአሁኔ ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘመን መሆኑን የገለጹት ወጣቶቹ መማር፣ መዘጋጀትና ከወቅቱ ጋር መጓዝ የግድ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በተለይም በክረምቱ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ዝግ በመሆናቸው ወጣቶች ጊዜያቸውን የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ እንዲጠቀሙበት አስገንዝበዋል። የክልሉ የመረጃ ማዕከል አስተዳደር ዳይሬክተር አብዲአዚዝ አብዲላሂ፤ የኢትዮ ኮደርስ ስለጠና እድሜ ሳይገድበው ለሁሉም ዜጎች በነፃ የሚሰጥ የዲጂታል እውቀት በመሆኑ ሁሉም እድሉን እንዲጠቀምበት መክረዋል። በተለይም ወጣቶች ዘመኑ የሚጠይቀውን ቴክኖሎጂ እውቅት በማዳበር ብቁና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ስልጠናው በእጅጉ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ እስካሁን ከ48ሺህ በላይ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው ሰርተፊኬት የተሰጣቸው መሆኑን ገልጸው በክረምቱ በእረፍት ላይ የሚገኙ ወጣቶች ሁሉ የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።
ስፖርት
ድራማዊ ክስተቶችን ባስተናገደው አስገራሚ ጨዋታ ፒኤስጂ ባየር ሙኒክን በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል
Jul 5, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ተጠባቂ መርሃ ግብር ፒኤስጂ ባየር ሙኒክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሜርሴዲስ-ቤንዝ ስታዲየም ዴዚሬ ዱዌ በ78ኛው እና ኡስማን ዴምቤሌ በ96ኛው ደቂቃ የማሸነፊያዋን ጎል አስቆጥረዋል። ጠንካራ ፉክክር በተደረገበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ለግብ የቀረቡ በርካታ እድሎች ፈጥረዋል። የፒኤስጂው ግብ ጠባቂ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ እና የባየር ሙኒክ ግብ ጠባቂ ማኑኤል ኖየር ግብ የሚሆኑ ኳሶችን በአስደናቂ ሁኔታ አድነዋል። የፒኤስጂ ተከላካዮች ዊሊያን ፓቾ እና ሉካስ ሄርናንዴዝ በፈጸመው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል። በጨዋታው ባየር ሙኒክ ሁለት ግቦችን አስቆጥረው ከጨዋታ ውጪ በመሆናቸው ተሽረዋል። በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ ፍጹም ቅጣት ምት አግኝቶም በቪዲዮ የታገዘ ዳኝነት (ቫር) ተሽሯል። በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ማብቂያ የባየርሙኒኩ የክንፍ ተጫዋች ጀማል ሙሲያላ ከፒኤስጂ ግብ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ ጋር በመጋጨቱ ምክንያት በግራ እግሩ ቁርጭምጭሚት ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዶ ተቀይሮ ወጥቷል። የተጫዋቹ አሰቃቂ ጉዳት በሁለቱ ቡድኖች ተጫዋቾች ከፍተኛ ድንጋጤ እና ፍርሃት ፈጥሮ ነበር። ሙሲያላ ወደ ሆስፒታል በማምራት ህክምናውን እየተከታተለ ይገኛል። ጉዳቱ ተጫዋቹን ለረጅም ጊዜ ከሜዳ ሊያርቀው ይችላል። ለ102 ደቂቃዎች የቆየው ጨዋታ አዝናኝ፣ ልብ አንጠልጣይ እና በክስተቶች የተሞላ ነበር። ውጤቱን ተከትሎ የአውሮፓ ሻምፒዮኑ ፒኤስጂ ለግማሽ ፍጻሜ አልፏል። ቡድኑ ከሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ አሸናፊ ጋር ይጫወታል። የመጨረሻው የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ በሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ መካከል ምሽት 5 ሰዓት ላይ በሜትላይፍ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
መንግስት ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንቢያ ከፍተኛ ሀብት ከመመደብ ጀምሮ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል
Jul 5, 2025 58
ባሕርዳር፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንቢያና እድሳት ከፍተኛ ሀብት ከመመደብ ጀምር ለስፖርቱ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለጹ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የሚያዘጋጀው ስለኢትዮጵያ ምዕራፍ ሁለት፣7ኛ መድረክ "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር " በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በባሕርዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ተካሂዷል። በመድረኩ ማጠቃለያ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ጋር በባሕር ዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።     ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ በመድረኩ ማጠቃለያ እንዳመለከቱት፤ እንደ ሀገር በሌሎች ዘርፎች ላይ የታቀዱ ዕቅዶችን ለማሳካት ጠንካራና በስፖርት የዳበረ ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት ስፖርት ያለውን አስተዋጽኦና ሚና በመገንዘብ መንግስት ለዘርፉ ልማት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል።   ለዚህም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጀምሮ ከፍተኛ የሀገሪቱ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች በሄዱበት አካባቢ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በማበረታታት ድጋፍ እየሰጡ መሆኑን አንስተዋል። ስፖርት በተባበረ ክንድ ሀገርን ለመገንባትና ህብረብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር የሚያስችል እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሯ፤ ይህንን ከግምት ያስገቡ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ለዚህም መንግስት የስፖርትን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ከግምት ያስገባ ከታች ጀምሮ እስከ ፌደራል ድረስ ከፍተኛ የሆነ ሀብት በመመደብ ስፖርታዊ ውድድሮች እንዲጠናከሩ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንዲገነቡና እድሳት እንዲያገኙ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። "አሸናፊ ስነ-ልቦናና ሀገረ መንግስት ግንባታ"በሚል ርዕስ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ በበኩላቸው እንዳሉት፤ እንደመንግስት የስፖርት መሰረተ ልማት በመገንባት ከፍተኛ የሆነ ትኩረት ሰጥቷል።   ስፖርት የስፖርታዊ እንቅስቃሴ ብቻ ሳይሆን የሀገር መገንቢያ ኃይል አንዱ ትልቅ መሳሪያ ነው ተብሎ ተለይቶ እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል። የስፖርቱ ማህበረሰብ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ሚና እንዲኖረው የተደራጀ ስራ መከናወን እንዳለበት አመልክተዋል። ለዚህም ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አንስተው፤ ለዘርፉ እድገት ሚዲያውን ጨምሮ ሁሉም አካል የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል። ኢንስትራክተር አብረሃም መብራቱ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በአለም ኦሎምፒክ፣ በፊፋና በካፍ ተሰሚነት ያላቸው ትልልቅ ሰዎችን ያፈራች ሀገር ናት።   አሁን ላይ የክለቦች አወቃቀር ዘመናዊና ወቅታዊ ያለመሆንና የመልካም አስተዳደር ክፍተት እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቀ አለመሆን የዘርፉ መሰናክሎች መሆናቸውን አንስተዋል። እንደ ሀገር ለስፖርቱ በፖሊሲ ደረጃ የተሰጠው ትኩረት ከሌሎች አገራት የተሻለና ሊያሰራ የሚችል እንደሆነም አብራርተዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ጋር በባሕር ዳር አለም አቀፍ ስታዲዮም ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል። በመድረኩ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የስፖርት ባለሙያዎች፣አሰልጣኞችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን፤ ስፖርትን የተመለከተ አውደ ርዕይም ለእይታ ቀርቧል።  
የዲያጎ ጆታ እና ወንድሙ አንድሬ ሲልቫ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈጸመ 
Jul 5, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦ ፓርቹጋላውያኑ የእግር ኳስ ተጫዋች ዲያጎ ጆታ እና የወንድሙ አንድሬ ሲልቫ የቀብር ስነ ስርዓት በሰሜናዊ ፓርቹጋል በምትገኘው የትውልድ ስፍራቸው ጎንዶማር ዛሬ ተፈጽሟል።   በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ የሊቨርፑል አሰልጣኝ አርን ስሎት፣ የቡድኑ አምበል ቨርጂል ቫን ዳይክ፣ አንድሪው ሮበርትሰን እና በርካታ የሊቨርፑል ተጫዋቾች፣ የፓርቹጋል አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ እንዲሁም የብሄራዊ ቡድን አጋሮቹ ብሩኖ ፈርናንዴዝ፣ በርናርዶ ሲልቫ፣ ሩበን ኔቬስ፣ ሩበን ዲያዝ እና ጆአ ካንሴሎ እንዲሁም የቀድሞ የቡድን አጋሮቹ፣ የተለያዩ ክለቦች አመራሮች እና ቤተሰቦቹ ተገኝተዋል።   ትናንት በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ በፍሉሜኔንሴ 2 ለ 1 የተሸነፈው የአል ሂላል ቡድን ስብስብ ውስጥ የነበሩት የቅርብ ጓደኛው ሩበን ኔቬስ እና ጆአ ካንሴሎ ከአሜሪካ ወደ ፓርቹጋል በመብረር ስርዓተ ቀብሩ ላይ ታድመዋል። ከቀብሩ ስነ ስርዓት ጎንዶማር በሚገኘው ማዘር ቤተ ክርስቲያን የአስክሬን ሽኝት ተደርጓል፡፡   ዲያጎ ጆታ እና ወንድሙ አንድሬ ሲልቫ ከትናንት በስቲያ ማለዳ ላይ በማድሪድ ግዛት በሰሜናዊ ፖርቹጋል ወደ ምትገኘው ጋላሲያ ከተማ እያቀኑ ባሉበት ወቅት በሰሜን ምዕራብ ስፔን በምትገኘው ዛሞራ ከተማ በደረሰው ድንገተኛ አደጋ ህይወታቸው አልፏል። ተጫዋቾቹ ሲጓዙበት የነበረው ላምቦርጊኒ መኪና ሌላ አልፎ ለመሄድ በሚሞክርበት ጊዜ የጎማ መፈንዳት አጋጥሞ መንገድ ስቶ የወጣው መኪና በእሳት በመያያዙ አደጋው ደርሷል። የሊቨርፑሉ ዲያጎ ጆታ በ28 ዓመቱ እና በፓርቹጋል ሁለተኛ ዲቪዚዮን ፔናሲፌል ቡድን ሲጫወት የነበረው አንድሬ ሲልቫ በ25 ዓመቱ ህይወታቸው አልፏል። ዲያጎ ጆታ ከአደጋው መከሰት ቀናት በፊት ከረጅም ጊዜ አጋሩ ሩት ካርዶሶ ጋር ጋብቻ መፈጸሙ የሚታወስ ነው።   በተጨማሪም በቅርቡ ከፓርቹጋል ጋር የዩኤፋ ኔሽንስ ሊግ እና ከሁለት ወር ገደማ በፊት ከሊቨርፑል ጋር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አንስቷል። ሊቨርፑል የዲያጎ ጆታን 20 ቁጥር ማልያ በክብር የሰቀለ ሲሆን የጆታን የሁለት ዓመት ኮንትራት ደሞዝ ለቤተሰቡ እንደሚከፍል አስታውቋል። ቡድኑ የቅድመ ውድድር ዝግጅት መጀመሪያ ጊዜውንም አራዝሟል። የዲያጎ ጆታ እና የወንድሙ አንድሬ ሲልቫ ሞት በዓለም እግር ኳስ ውስጥ ትልቅ ድንጋጤን የፈጠረ ሲሆን ፖርቹጋልን ጥልቅ ሀዘን ውስጥ ከቷል።   ያሏቸውን ሁለት ልጆች ያጡት እናት እና አባቱ እንዲሁም ባሏን ያጣቸው ሩት ካርዶሶ ሁኔታ እጅጉን አሳዛኝ ሆኗል። የዓለም እግር ኳስ ማህበረሰብ ለወንድማማቾቹ ቤተሰቦች እና ወዳጆች ሀዘኑን በመግለጽ ላይ ይገኛል። ዲያጎ ጆታ የሶስት ልጆች አባት ነበር።
የስፖርቱን ዘርፍ ይበልጥ ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Jul 5, 2025 60
ባሕርዳር ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፡-ምቹ የስፖርት ሜዳዎችን ከመገንባት ጀምሮ የስፖርቱን ዘርፍ ይበልጥ ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የሚያዘጋጀው ስለ ኢትዮጵያ ምዕራፍ ሁለት 7ኛ የፓናል ውይይት መድረክ "ስፖርት ለአሸናፊ ሀገር " በሚል መሪ ሀሳብ በባሕር ዳር አለም አቀፍ ስታዲየም እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የስፖርት ባለሙያዎች፣አሰልጣኞችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።   የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ የፓናል ውይይቱ ሰጀመር ባደረጉት ንግግር እንዳሉት፤ ስፖርት ብቁና ንቁ ዜጋ ለመፍጠር የሚያግዝ የውድድር መድረክ ነው። ስፖርት ህብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት ከንግግር ባለፈ በተግባር የሚገልጽና ሀገራዊ ስሜት የሚንፀባረቅበት ሰላማዊ ውድድር መሆኑን ገልጸዋል። በስፖርት ልማት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ከማህበራዊ ዘርፉ በላይ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውም የጎላ በመሆኑ የግል ባለሀብት ጨምሮ ሁሉም አካል በዘርፉ ልማት ላይ ሊሳተፉ እንደሚገባ አመልክተዋል። የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ በበኩላቸው፤ መንግስት የስፖርት ዘርፉን ሁለንተናዊ ፋይዳ በመረዳት ትኩረት ሰጥቶ እየደገፈ እንደሚገኝ ተናግረዋል።   ምቹ የስፖርት ሜዳዎችን ከመገንባት ጀምሮ ለስፖርት ዘርፉ ዕድገት አስቻይ ሁኔታዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከፓናል ውይይቱ በተጓዳኝ የስፖርት ዘርፍን የተመለከተ የፎቶ አውደ ርዕይም ተከፍቷል።
አካባቢ ጥበቃ
በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም በንቃት በመሳተፍ አሻራውን ሊያኖር ይገባል
Jul 5, 2025 45
ሶማሌ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፡- በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም በንቃት በመሳተፍ አሻራውን ሊያኖር ይገባል ሲሉ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ገለጹ። የክልሉ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እና አረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ርእሰ መስተዳድሩ በተገኙበት በጅግጅጋ ከተማ ተካሂዷል።   በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ፤ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ ልማትን ጨምሮ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት አመታት በተከናወኑ ስራዎች አካባቢን በመጠበቅና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ሂደት ስኬቶች መታየታቸውን አንስተዋል። በመሆኑም በዘርፉ ልማት ዘንድሮም ዝግጅት መደረጉን ገልጸው በመርሃ ግብሩ ሁሉም በነቂስ በመሳተፍ አሻራውን እንዲያሳርፍ አስገንዝበዋል።   ከችግኝ ተከላ በተጨማሪ በክረምት በጎ ፈቃድ የአረጋውያንና አቅመ ደካሞችን ቤት በማደስና በመገንባት፣ በአካባቢ ጥበቃ፣በደም ልገሳ እና ሌሎችም መስኮች ነፃ አገልግሎቱ እንዲጠናከር አፅእኖት ሰጥተዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል።
የአረንጓዴ አሻራ ልማትን ዘርፈ ብዙ ጥቅም በተግባር የተገነዘብን በመሆኑ ችግኞችን ለመትከል እና ለመንከባከብ ተዘጋጅተናል
Jul 5, 2025 60
አሶሳ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ ልማትን ዘርፈ ብዙ ጥቅም በተግባር የተገነዘብን በመሆኑ ችግኞችን ለመትከል እና ለመንከባከብ ተዘጋጅተናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ። የ2017 የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በክልሉ በኡራ ወረዳ ሰልጋ 20 ንዑስ ተፋሰስ ልማት ላይ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ ከተገኙት መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የአረንጓዴ አሻራ ልማትን ዘርፈ ብዙ ጥቅም በተግባር የተገነዘብን በመሆኑ ችግኞችን ለመትከል እና ለመንከባከብ ተዘጋጅተናል ብለዋል። ካነጋገርናቸው መካከል አቶ አብዱላሂ ሙሀመድ እና ወይዘሮ ሺዋጋ አለሙ፤ የአረንጓዴ አሻራ ውጤት ምግብም፣ ጥላና ከለላም እየሆነ እኛንም ተፈጥሮንም እየጠበቀ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል። በአካባቢያቸው መሬት እንዲያገግም እና ለእንስሳት መኖ በቅርበት እንዲያገኙ እያደረገም ስለመሆኑ አንስተዋል። በተለይም በተፋሰስ ልማት ላይ የሚተከሉ ችግኞች የመጽደቅ መጠናቸው ከፍተኛ በመሆኑ የተፋሰስ ልማት እና የችግኝ ተከላን በተጠናከረ መልኩ የሚያስቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል።     ሌላው በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት መቶ አለቃ በሱፍቃድ ገላን፤ የመከላከያ ሰራዊት የሀገርን ዳር ድንበር ከማስጠበቅ ባለፈ በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ የነቃ ትብብርና ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም መሰረት የልማት አጋር በመሆን በዛሬው እለት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሻራቸውን ማኖራቸውን ገልጸዋል።   በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተሳተፈችው ተማሪ ፎዚያ ሙሀመድ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለትውልድ የሚተርፍ አሻራ በመሆኑ የዚሁ ታሪክ አካል ለመሆን ተገኝቻለሁ ብላለች። በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ርእሰ መስተዳደር አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች፣ የፀጥታ አካላት እና የአካባቢው ማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተው አሻራቸውን አኑረዋል።
በለውጡ ዓመታት ለአረንጓዴ አሻራ ልማት የተሰጠው ትኩረት የተራቆቱ አካባቢዎችን እየለወጠ ነው- አቶ አሻድሊ ሃሰን
Jul 5, 2025 50
አሶሳ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ)፦በለውጡ ዓመታት ለአረንጓዴ አሻራ ልማት የተሰጠው ትኩረት የተራቆቱ አካባቢዎችን እየለወጠ እንደሚገኝ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሃሰን ገለጹ። በክልሉ እየተከናወነ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የህዳሴ ግድብን ከደለል በመከላከል ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑንም ርዕሰ-መስተዳድሩ ተናግረዋል። ዛሬ በክልሉ ኡራ ወረዳ ሰልጋ 20 ንዑስ ተፋሰስ ልማት ላይ በተከናወነው የ2017 የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ ርዕሰ-መስተዳድሩ እንደገለጹት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከተጀመረ በኋላ በአካባቢው ስነ-ምህዳር ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል። በክልሉ እየተከናወነ ያለው ተከታታይ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከልማትም ባለፈ የህዳሴ ግድብን ከደለል በመከላከል ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ገልጸዋል።   በለውጡ ዓመታት በተለይም ለአረንጓዴ አሻራ ልማት በተሰጠው ልዩ ትኩረት በርካታ የተራቆቱ አካባቢዎች እየለሙ መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት ዓመታት የተተከሉ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ፍሬ እየሰጡ በመሆኑ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥና የአካባቢ ጥበቃን በማጠናከር ውጤት መጥቷል ሲሉም ተናግረዋል። የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ የተጀመረ ሲሆን በክልሎችም በተጠናከረ መልኩ ቀጥሏል። በመሆኑም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም በዛሬው እለት በይፋ መጀመሩን ተከትሎ የክልሉ ህዝብ በትጋት አረንጓዴ አሻራውን ለማሳረፍ እንዲነሳሳ ርእሰ-መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ባበክር ሀሊፋ፤ በክልሉ አብዛኛው ተፋሰሶች ከህዳሴ ግድብ ጋር የሚያያዙ በመሆናቸው የሚተከሉ ችግኞች ህዳሴ ግድብን ከደለል ለመጠበቅ ፋይዳቸው የጎላ ነው ብለዋል።   እስከ አሁን በ47 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ሲከናወን መቆየቱን የገለፁት ኃላፊው የተፋሰስ ልማት በተከናወነበት አካባቢ ደግሞ ችግኞች በብዛት የሚተከሉ መሆኑን ተናግረዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩ በየደረጃው ያሉ የክልሉ አመራሮች፣ የፀጥታ አካላት፣ ወጣቶች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
የአረንጓዴ አሻራ ልማቱ እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመውጣት ለሚደረገው ጥረት ፋይዳው የላቀ ነው
Jul 5, 2025 51
ጋምቤላ ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ) ፦የአረንጓዴ አሻራ ልማቱ እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመውጣት ለሚደረገው ጥረት ፋይዳው የላቀ መሆኑን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። ''በመትከል ማንሰራራት'' በሚል መሪ ሀሳብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ በይፋ የተጀመረው የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሎችም ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዚህም በዛሬው እለት በጋምቤላ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ፤ በተገኙበት በክልል ደረጃ የአረንጓዴ አሻራ ልማት በይፋ ተጀምሯል።   ርዕሰ መስተዳድሯ አሻራቸውን ካኖሩ በኋላ ባስተላለፉት መልእክት የአረንጓዴ አሻራ ልማቱ እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመውጣት ለተጀመሩ ጥረቶች ጉልህ ድርሻ አለው ብለዋል። በዚህም መሰረት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ በክልሉ በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉን አንስተው በልማቱ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በብዛት የሚተከሉ መሆኑን ተናግረዋል።   ከመትከልም ባለፈ ለጽድቀታቸው በመንከባከብና በመጠበቅ ለአገልግሎት እንዲበቁ ማድረግ የሁሉም አደራና ሃላፊነት እንዲሆን ርእሰ መስተዳድሯ ጠይቀዋል። የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፓል ቱት፤ የአረንጓዴ አሻራ ልማቱ የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትን ለመቀነስና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ ባለፉት ተከታታይ አመታት በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አጋዥ መሆኑንም ተናግረዋል።   በዚህ ዓመት ለተከላ ከተዘጋጁት ችግኞች 60 በመቶ የሚሆኑት የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን ጠቁመው ከ7 ሺህ ሄክታር በላይ የተራቆቱ መሬቶችን በስነ-ህይወት የማላበስ እቅድ ተይዟል ብለዋል። በዛሬው እለይ በይፋ የተጀመረው ክልል አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ለቀጣይ ሁለት ወራት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ታውቋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 630
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ።   በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1152
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል።   የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 836
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል።   ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1458
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
የህንድ የፈጠራ ማዕከል - ባንጋሎሩ
Jul 2, 2025 167
ቤተልሄም ባህሩ(ኢዜአ) የዴልሂና አግራ ቆይታችንን ጨርሰን ወደ ቀጣይ መዳረሻችን ባንጋሎሩ ከተማ ልንጓዝ ስንሰናዳ አብዛኛው የጋዜጠኛ ልዑክ ያሳሰበው እንደሰም የምታቀልጠውን የአግራ ፀሀይና ሙቀት በባንጋሎሩም ታገኘን ይሆን? የሚለው ነበር። ሆኖም ከዴልሂ ኢንድራ ጋንዲ አየር ማረፊያ ተነስተን ለሶስት ሰዓት ከተቃረበ በረራ በኋላ ያገኘናት ባንጋሎሩ የተለየች ሆነን አገኘናት። ባንጋሎሩ ቀዝቀዝ ባለ አየር ነበር እንግዶቿን የተቀበለችን። በዕለቱ ከክፍሎቻችን ወጥተን በጋራ ወደአየር ማረፊያ የሚወስደንን ትራንስፖርት ስንጠባበቅ ከጋዜጠኛ ቡድኑ ስድስት አባላት ከአጠገባችን እንዳልነበሩ አስተዋልን። የት ጋር እንደተነጣጠልን አላስታውስም። በዚህ ምክንያት ግን የእለቱ ጉዟችን ተሰርዞ ከተማዋን ለማየት ስንዘዋወር የማውቀው ዓይነት እንጂ የተለየ ሙቀት አላስተናገድኩም። የ13 ወር ፀጋ በመባል የምትታወቀው አገሬ ኢትዮጵያ ከዳሎል እስከ ራስ ዳሽን ባላት የመልከዓ ምድር አቀማመጥና ልዩ ልዩ የአየር ጠባይ ሙቀቱንም፣ ቅዝቃዜውንም ማወቃችን እንደዚህ ለአለ አጋጣሚ መልካም ስሜት ይፈጥራል። በተወሰነ ደረጃ በህንድ ያጋጠመኝ የአየር ባህሪ ከአገሬ ጋር ቢመሳሰልብኝ የፈጣሪንና የተፈጥሮን ስራ አጃኢብ ብዬ እንዳልፍ አድርጎኛል። ባንጋሎሩ ከተማ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የህንድ ሲልከን ቫሊ በመባል ትታወቃለች። ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎችም ከመገለጫዎቿ መካከል ናቸው። የጠፈር ጠበብቶቹ - ባንጋሎሩ ደርሰን በመጀመሪያ ያየነው ዓለም በስፔስ ሳይንስ እየሰራች ያለችውና እያስመዘገበችው የምትገኘው ውጤት ማሳያ የሆነውን የህንድ ስፔስ ምርምር ድርጅትን ነው። ተቋሙ የህንድ መንግስት የስፔስ ዲፓርትመንት አካል ሲሆን፤ ዶክተር ቪክራም ሳራብሃይ በተሰኙ ባለራዕይ በ1962 የተወጠነና አሁን ላይ በዘርፉ ተገዳዳሪ መሆን የቻለ ነው። የተቋሙ ዓላማ የስፔስ ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመተግበር ለተለያዩ አገራዊ ጥቅሞች ማዋል መሆኑን ተከትሎ የሳተላይት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማምረት ስራን ጨምሮ ከአገሩ አልፎ ለሌሎች አገራትም በዘርፉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። የተደረገልን ገለፃ አብዛኛውን ጋዜጠኛ ያስደመመ ነበር ከገለፃ በኋላ በጋዜጠኞች የተነሳው ሃሳብም ህንድ በስፔስ ዘርፍ ያላት ልምድና ያከናወነችው ተግባር በቀጣይም ልትሰራ የወጠነቻቸው ሃሳቦች የአገሪቱን መዳረሻ የተለሙ በአገራቸው እንዲተገበር የሚናፍቁት መሆኑን ነው። ተቋሙ በዘርፉ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን የሚያጠናክር መሆኑን ከተደረገልን ገለፃ ተገንዝበናል።   በሳይንስ፣ ኢንጂነሪንግና አስተዳደር ምሁራንን በማስተማር እያበረከተ ያለው የህንድ የሳይንስ ኢንስቲትዩት በባንጋሎሩ ከጎበኘናቸው መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የተውጣጡ ተማሪዎችን የሚያስተምርና ከተቋማት ጋርም በዘርፉ የሚሰራ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ከጅማ፣ በተግባር ለመቀየር ሲታትሩ የስታርት አፖችን የምርት ውጤቶቻቸውን ሲፈትሹና ሲሞክሩ ተመልክቻለሁ። በኢትዮጵያም አሁን ላይ ለስታርት አፖች በተሰጠው ትኩረትና በተፈጠረው ምቹ ስነ ምህዳር የፈጠራ ውጤቶች እያደጉና እየተበራከቱ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። እንደ አዳማና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት የተማሪዎችን ፈጠራ ወደ ውጤት ለመቀየር እየተጉ መሆኑና የስታርት አፕ ኤግዚቢሽንና የሰመር ቡት ካምፖች ፈጠራን ምን ያህል እያበራከቱ መሆናቸው በጉብኝቱ ወቅት ወደ አዕምሮዬ የመጣ የአገሬው ህዝብ በውጤት የታጀበ ጥረት ነው።   ከአራት አስርት ዓመታት በላይ በባዩቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘው ባዮኮንም ከባላንጎሩ የጉብኝት መዳረሻችን መካከል የሆነና አስፈላጊ መድሀኒቶችን የሚያመርትና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይም እየሰራ ያለ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተጠቃሚ ናቸው። ከ120 በላይ በሆኑ አገራት ለስኳርና ካንሰር ህመም የሚያገለገሉ መድሀኒቶችን በማምረትና በማሰራጨት ለህሙማን ፈውስና ለጤናው ዘርፍ ስርዓት አስተዋፅኦ እያበረከተም ይገኛል። የተቋሙ ላቦራቶሪና ዘመኑን የዋጀና ደረጃውን የጠበቀ ማምረቻ ፋብሪካን መጎብኘቴ አለም በፋርማሲዩቲካልስ ዘርፍ ያለችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። የባንጋሎሩ ቤተመንግስት - ይህን ቤተ መንግስት ማስቃኘቴን ከመጀመሬ በፊት በስፍራው ካስገረመኝ ነገር ላወጋችሁ ወደድኩ። ቤተ መንግስቱን ለመጎብኘት ያቀናነው በእለተ ሰኞ ነበር። ሆኖም ምድረ ግቢውን ቃኝተን ስለህንፃው ሰምተን ከመመለስ ውጪ ወደ ውስጥ አልዘለቅንም። ለምን? ለሚለው ምላሹ በዚህ ስፍራ "ሰኞ የእረፍት ቀን ናት" ነው። እንዴት ካላችሁ ቤተ መንግስቱ ቅዳሜና እሁድ በበርካታ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑን ተከትሎ በስፍራው ለሚሰሩ ሰራተኞች የእረፍት ቀናቸው ሰኞ በመሆኑ ነው። የቤተ መንግስቱ ምድረ ግቢ ሰፊና ልምላሜ የተላበሰ ሲሆን፤ የሚያምርና ለዓይን የሚስብ ኪነ ህንፃ ያለው ነው። አሰራሩና ውጥኑም እንደሚከተለው ነው። በዎዲየር ስርወ መንግስት ንጉስ ቻማራጃ ዋዲያር ወደ እንግሊዝ ባደረጉት ጉዞ በለንደን ዊንሶር ግንብ ይደነቃል። ተደንቆም አልቀረ የባንጋሎሩ ቤተ መንግስትን በተመሳሳይ ሁኔታ ይገነባል። ይህ ቤተ መንግስት በተወሰነ መልኩ የመካከለኛው ዘመን የኖርማንሲና የእንግሊዝ ግንቦችን ይመስላል።   ቪድሃና ሶውዳ የካራንታካ ህግ አውጪ አካል መናገሻ በጉብኝታችን ያየነው ሌላው መዳረሻ ስፍራችን ነው። የህግ አውጪና የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የያዘው ይህ ህንፃ ህንድ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ በራሷ መሀንዲስ የሰራችው የመጀመሪያው ህንፃ መሆኑ ተገልፆልናል። የህንፃ ግንባታ ጥበብ ማሳያ፣ የፖለቲካ መናገሻ እንዲሁም የባህል ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል።   እንደአጠቃላይ በቆይታዬ የተመለከትኩት የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ማበረታቻ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራ ኢትዮጵያ እያከናወነች ካለው የኮሪደር ልማትና ስታርት አፕን የማበረታታት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ምቹነት ስራዎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ነው። በህንድና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ዘመናትን የተሻገረ፤ ለሁለት ሺህ ዓመታት የዘለቀ መሆኑን የታሪክ መዛግብት ያሳያል። የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት በአክሱም ስርወ መንግስት ኢትዮጵያና ህንድ በአዱሊስ ወደብ በኩል የንግድ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያ ቅመማ ቅመምና ሐርን ከህንድ ትገበይ ነበር። ህንድ ደግሞ ወርቅና የዝሆን ጥርስን ከኢትዮጵያ ትሸምት ነበር። ህንድ ከንግድ ልውውጥ ባሻገር በኢትዮጵያ ኪነ ህንፃ ግንባታ ላይ አሻራዋን አኑራለች። በኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍም ትልቅ አበርክቶ ያላት አገር ናት። ህንድ ነፃነቷን ካገኘችበት እኤአ 1948 አንስቶ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት ኢትዮጵያና ህንድ ሌላው የሚያመሳስላቸው ነገር ሆኖ ያገኘሁት የአምራች ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያከናወኑ ያሉት ንቅናቄ ነው። ህንድ እ.አ.አ ከ2014 ጀምሮ የአምራች ዘርፉን ለማበረታታት "ሜድ ኢን ኢንዲያ" በሚል ለአስር ዓመት የተገበረችውና በርካታ ለውጥ የተመዘገበበት ንቅናቄ በኢትዮጵያ ከ2014ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ካለውና የሃገር በቀል ምርቶች እና አምራቾችን ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪያል ማህበረሰብ ግንባታን ማሳደግ ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢ መፍጠር እና የጥናት እና ምርምር ችግር ፈቺነትን ማሳደግን ዓላማ ካደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጋር የተመሳሰለ ነው። ንቅናቄ በኢትዮጵያ መተግበሩ ዓመታዊ የዘርፍ ዕድገት፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና ገቢ ምርት በመተካት በኩል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑም ይታወቃል። በህንድ ተዘዋውሬ በተመለከትካቸው ከተማዎች ባሉ ጎዳናዎች ከታዘብኩት ነገር ሰዎች ከሱቅ ለሚገበያዩት ነገር ሳይቀር በዲጂታል መንገድ ክፍያ መፈፀማቸውን ነው። በባጃጅና በሞተር የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘትም ጭምር ሞባይሉን በመጠቀም “ይህ ቦታ የት ነው?” ሳይል ያሻዎት ስፍራ መድረስም ሌላው ትዝብቴ ነው። ይህ ነገር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትኩረት አግኝተው እየተሰራባቸው ካሉት የዲጂታል ክፍያና ዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ መርሃ ግብር ጋር የሚመሳሰል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በቆይታችን ልክ እንደአትሌቶቻችን ሁሉ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርጎ የሚያስነሳውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝናና ክብር ለማስተዋል ችያለሁ። ፀጉረ ልውጥ መሆናችንን የተገነዘቡ በገበያ ማዕከላት የሚያገኙን እንዲሁም በምንጎበኛቸው ተቋማት የምንተዋወቃቸው ህንዳውያን "ከየት ናችሁ?" ብለው ሲጠይቁ፤ ለእኔና አንድ ከሌላ መገናኛ ብዙሃን የሄድን "ከኢትዮጵያዊ" ስንል የሚከተልልን ምላሽ "አሃ የኢትዮጵያ አየር መንገድ" የሚል ነው። ይህም አየር መንገዱ ስሙ ከኢትዮጵያ ተሰናስሎ የሚጠራ የአገሪቷ መታወቂያ ተቋም መሆኑን ያስገነዘበኝ ነው። ከህንዳውያን ጋር ብቻ ሳይሆን አብረን ከተጓዝን ጋዜጠኞች አንዱ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእናንተ የብቻ ሳይሆን እኛንም እንደራሳችን ሆኖ እያገለገለን ያለ የጋራ አየር መንገዳችን ነው" ሲል ነው የገለፀው። ይሄ ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገር ኩራት ብቻ ሳይሆን መለያ ምልክትም ጭምር መሆኑን የተረዳሁበት አጋጣሚ ነው። በቀናት ቆይታዬ በእንግዳ አክባሪነታቸውና በለገሱን ፍቅርና እንክብካቤ ከአገሬ የራቅኩ ያህል ሳይሰማኝ ብቸኝነትን ሳላስተናግድ እንደውም እየናፈኳቸው እንድመለስ ላደረጉኝ ህንዳውያን በከበረ ሰላምታ ላመሰግን እወዳለሁ።
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 315
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል።   ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል።   የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው።   የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው።   ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።    
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 857
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች።   የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች።   ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ።   ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።      
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 973
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 3106
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 2630
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2832
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 3947
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2433
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2243
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3683
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48118
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43611
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 27927
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25274
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 23524
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 21682
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 21512
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 21140
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48118
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43611
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 27927
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25274
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የዋጋ ንረት ምን ማለት ነው?
Jun 30, 2025 292
የዋጋ ንረት በንፅፅር ለምሳሌ አምና 26 በመቶ ዘንድሮ 14 በመቶ ሲሆን ምን ማለት ነው? ለምሳሌ የአንድን የ100 ብር ዕቃ ወስደን ብንመለከት ካቻምና ከነበረበት 100 ብር አምና 126 ብር ሆኖ ነበር ማለት ነው። ስለዚህ የዕቃው ዋጋ በአመት ብር 26 ጨምሯል ማለት ነው። በተመሳሳይ መንገድ አምና 100 ብር ዋጋ ያለው ዕቃ ዘንድሮ 14 በመቶ ካደገ ዘንድሮ 114 ብር ይሆናል ማለት ነው። በዚህ ስሌት የዕቃው ዋጋ ካምና ወደ ዘንድሮ የጨመረው በ14 ብር በመሆኑ አምና ከጨመረበት ብር 26 ጋር ሲነፃፀር ጭማሪው ቀንሷል ማለት ነው። ዋጋን ያየን እንደሆነ ግን 100 ብር የነበረ ዕቃ 114 በመሆኑ ጨመረ እንጂ አልቀነሰም። የዋጋ ንረት ጨመረ የሚባለው ደግሞ ለምሳሌ አምና 26 በመቶ የጨመረው ዘንድሮ 14 በመቶ ሳይሆን 30 በመቶ ቢሆን የጨመረው አምና 100 ብር የነበረው ዕቃ ዘንድሮ 114 ሳይሆን 130 ብር ይሆናል ማለት ነው። ይህ አምና ከጨመረበት የ26 ብር ይበልጣል ማለት ነው። ስለዚህ ካቻምና 100 ብር የነበረው ዕቃ አምና 26 ብር ጨምሮ 126 ከሆነ በኋላ ዘንድሮም 14 ብር ስለጨመረ በቀላል ቀመር ዘንድሮ 140 ብር ሆኗል ማለት ነው። ስለዚህ በሁለት አመታት የዕቃው ዋጋ 40 ብር ጨምሯል። የዕቃው ዋጋ አልቀነሰም በየአመቱ የጨመረበት ምጣኔ ግን ካምና ዘንድሮ ያነሰ ነው። ይህ ነው የዋጋ ንረት ቀነሰ ማለት። ዋጋ ቀነሰ ማለትስ ምን ማለት ነው? ዋጋ ቀነሰ የሚለውን ከማየት በፊት የዋጋ ንረት የለም ማለት ምን እንደሆነ በዛው 100 ብር ዋጋ ባለው ዕቃ እንመልከት። ይህ ባለፈው አመት ብር 100 የነበረ ዕቃ ዘንድሮም እዛው 100 ብር ላይ ቢቆይ የዋጋ ንረት ዜሮ ነው። ስለዚህ የዕቃው ዋጋ አልተለወጠም ማለት ነው። ዋጋ ቀነሰ ማለት ግን የዋጋ ንረት ከዜሮ በታች ይሆናል ማለት ነው። በምሳሌው ለማስረዳት አምና 100 ብር ዋጋ ያለው ዕቃ ዘንድሮ 90 ብር ቢሆን የዋጋ ንረቱ ወይም ለውጡ ከዜሮ በታች 10 በመቶ ነው። በዚህ ግዜ የዋጋ ንረት ቀነሰ ሳይሆን ዋጋ ቀነሰ ይባላል። እነዚህ ሶስቱ የዋጋ ለውጦች ለሸማቾችና ለአምራቾች ምን ማለት ናቸው? ለሸማቾች ከሁሉም የሚመረጠው ዋጋ ሲቀንስ ማለትም 100 ብር የነበረው ዕቃ 90 ብር ሲሆን ነው። በሁለተኛ ደረጃ ተመራጩ ዋጋ ንረት ሳይኖር አምና 100 ብር የነበረው ዕቃ ዘንድሮም ሳይለወጥ በዜሮ ንረት 100 ብር ላይ ሲቆይ ነው። ሶስተኛው የተሻለ አማራጭ አምና 100 ብር የነበረ ዕቃ ዘንድሮ በ26 በመቶ ጨምሮ ብር 126 ከሚሆን በ14 በመቶ ጨምሮ ብር 114 ሲሆን ነው። ይህ ሶሰተኛው አማራጭ በሁለቱም ዋጋ ስለሚጨምር በትንሽ የጨመረው ተመራጭ ይሆናል ማለት ነው። ከአምራቾች አንፃር ሲታይ ከላይ ለሸማቾች የተሻለ አማራጭ በቅደም ተከተል ያስቀምጥነውን ገልብጠው ማንበብ ነው። አሁን ብሔራዊ ባንክ እያለ ያለው የዋጋ ንረት ወይም አመታዊ ጭማሪው ቢበዛ ከ10 በመቶ እንዳይበልጥ የሚረዳ የገንዘብ ፖሊሲ እተገብራለሁ ነው። የባንኩ አላማ የዋጋ ንረት ዜሮ ወይም ከዜሮ በታች እንዲሆን ሳይሆን 1) ከ10 በመቶ በታች እንዲሆን ሲሆን 2) የትረጋጋና ተገማች እንዲሆን ነው። የተረጋጋ ማለት ከወር ወር ወይም ካመት አመት ዋጋ የሚለወጥበት ሁኔታ በጣም የተራራቀ ያልሆነ ማለት ነው። ለምሳሌ ካንዱ ወር ወደ ቀጣይ ወር ጭማሪው 0.5 በመቶ ሆኖ በቀጣይ ወር ደግሞ የ5 በመቶ ጭማሪ ከዚያም በቀጣይ ወር ከዜሮ በታች የ2 በመቶ ወርሃዊ ለውጥ ቢመዘገብ ያልተረጋጋ ወይም ተገማች ያልሆነ የዋጋ ለውጥ አለ ማለት ነው። ሰለዚህ የተረጋጋና ተገማች የዋጋ ለውጥ እንዲኖር ማድረግ የባንኩ ሁለተኛው አላማ ነው ማለት ነው። ብሔራዊ ባንክ በጣም ዝቅተኛ የዋጋ ንረት ወይም ከዜሮ በታች የዋጋ ለውጥ እንዴት ያየዋል ብለን ያየን እንደሆነ ነገሩ እንዲህ ነው። ቅድም ከላይ እንዳየነው የዋጋ ንረት ከሸማቾችና ካአምራቾች አንፃር የሚታየው በተቃራኒ መንገድ ነው። ስለሆነም ምንም እንኳን የዋጋ ንረት በጣም ዝቅተኛ ወይም ከዜሮ በታች ቢሆን ለሸማቾች ጥሩ ቢሆንም አምራቾችን ግን የማያበረታታ ስለሚሆን ማምረት ያቆማሉ ሠራተኛ ይቀንሳሉ አጠቃላይ የኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ይገታና ጭራሽ ከምርት እጥረት የተነሳ የዕቃዎች ዋጋ መናር ይከሰታል ሥራ አጥነት ይበዛል። ስለዚህ መንግስት ሥራ እንዲፈጠር ኢኮኖሚ እንዲነቃቃም ስለሚፈለግ የተረጋጋና ዝቅተኛ ሸማቹን የማይጎዳ አምራቹንም የሚያበረታተ የዋጋ ሁኔታ እንዲኖር ይሰራል ማለት ነው። ለአንድ ኢኮኖሚ ትክክለኛው የዋጋ ንረት ስንት ነው? ይህ ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ግን ከባድ ነው። ይህን ጥያቄ ለመመለለስ ከሚረዱት ሁኔታዎች አንዱ ኢኮኖሚው ያለበት ደረጃ ነው። ምን ማለት ነው በጣም ባደገና የበለጠ የማደግ እድሉ ጠባብ ለሆነ ኢኮኖሚ 1 በመቶ ወይም 2 በመቶ የዋጋ ንረት ከፍተኛ ሊሆን ይችላል። በአንፃሩ ደግሞ ገና የማደግ እምቅ አቅም ላለውና በማደግ ላይ ላለ ሀገር ነጠላ አሃዝ የዋጋ ንረት እንደ ሁኔታው የሚለያይ ሆኖ ተመራጭ ሊሆን ይችላል። ስንት ነው የሚለው ግን በሳይንሳዊ መንገድ መረጋገጥ አለበት። ለምሳሌ የሀገራችንን threshold inflation or optimal inflation level ለማወቅ እኔን ጨምሮ የባንኩ ሠራተኞች በሳይንሳዊ መንገድ ለማወቅ ተሞክሯል። በኔ ጥናት 7 በመቶ ሲሆን በሌሎቹም ከዚሁ ያልራቀ ውጤት እንዳለ አይቻለው የመረጃ አጠቃቀምና የሜቶዶሎጂ ልዩነቱ እንዳለ ሆኖ ማለቴ ነው። ሰለዚህ በነዚህ ጥናት መሰረት ብሔራዊ ባንክ የነጠላ አሃዝ የዋጋ ንረት አላማ አድርጎ መንቀሳቀሱ ትክክለኛ አቅጣጫ ነው ማለት ነው ለኛ ኢኮኖሚ። ለማጠቃለል የዋጋ ንረት ምንነትን በተመለከተ ያለውን ውዥምብር ለማጥራት ይህ አጭር መግለጫ ያግዛል ብዬ እያመንኩ የበለጠ መብራራት ካለበት ወይም ጥያቄ ካለ አንባቢዎች በአስተያየት መስጫው ላይ ማሰቀመጥ ትችላላችሁ። አቶ ፈቃዱ ደግፌ የብሔራዊ ባንክ ም/ገዥ
የሺህ ሀይቆች ምድር
Jun 24, 2025 499
የሺህ ሀይቆች ምድር (በራሔል አበበ) በርካታ መገለጫዎች አሏት። የሺህ ሀይቆች መፍለቂያ። አረንጓዴ ምድር። 75 በመቶ የአገሪቱ ገፀ-ምድር በደን የተሸፈነ። የአምስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ሕዝብ መኖሪያ። በአውሮፓ ከበለጸጉ አገራት አንዷ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለስምንት ተከታታይ ዓመታት በዓለም ቁጥር አንድ የደስተኞች አገር በመባል የተሰየመች ሰሜን አውሮፓዊት አገር - ፊንላንድ። በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋባዥነት በአዲስ አበባ የአገሪቱ ኤምባሲ አስተባባሪነት በቅርቡ ፊንላንድን የመጎብኘት ዕድል አግኝቼ ነበር። በጉብኝቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ የኬኒያ፣ ታንዛኒያ፣ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴኔጋል፤ ሞዛምቢክ እና ዛምቢያ ጋዜጠኞች ተሳትፈናል። የአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ነው። ምንም እንኳን የትም አገር ስሄድ ቀድሜ መረጃ የማየት ልምድ ቢኖረኝም በመጀመሪያው ዕለት ለእራት ስንወጣ ያየሁት በምሽት ያልተለመደ የፀሐይ ፍካት ግን እራቱ ቁርስ እንዲመስለኝ አድርጓል። ከዚያ በኋላ ለመድሁት። በእርግጥ በአንድ ወቅት በስፔንም ፀሐይ እስከ እኩለ ሌሊት የማትጠልቅበትን ክስተት ተመልክቻለሁ። በፊንላንድ ያየሁት ግን ተለየብኝ። ፀሐይ ፈጽሞ ለጨረቃ ቦታ መልቀቅ አትፈልግም። ምሽቱ የሚደምቀው በመብራት ሳይሆን በፀሐይ ነው። ሌሊቱ ብርሀን ነው። ሰማይ አይጠቁርም። በየዕለቱ ሳይጨልም ይነጋል። በዚህ ወቅት በተለያዩ የአውሮፓና የአሜሪካ አገራት ሰማይ ላይ የሚታየው ሰሜናዊ የቀለማት የብርሀን ፀዳል ሌላው የፊንላንድ መድመቂያ ነው። የሰሜን አውሮፓ/ኖርዲክ አገራት በተፈጥሮ የታደሉ ናቸው። እኔ ደግሞ የተፈጥሮ አድናቂ ነኝ። ያለማጋነን በፊንላንድ ተፈጥሮ ከነክብሯ ተጠብቃ አይቻለሁ። ንጹህ አየሯ የዚህ ውጤት ነው። አድናቆቴ የጀመረው ከኤርፖርት እስካረፍኩበት ሆቴል 15 ኪሎ ሜትር ያህል በመኪና ስንጓዝ የከተማዋን አረንጓዴነትና የምድሪቱን ልምላሜ ስመለከት ነበር። በጉብኝቴም በተግባር አረጋገጥሁ። የአገሪቱ አብዛኛው መሬት በደንና በውሃ ተሸፍኗል። በዋና ከተማዋ ሄልሲንኪና በዙሪያዋ በሚገኙ ውብ ደኖች መሀል ስንጓዝ መሬቱ ለም ስለመሆኑ ዓይን ብቻ ሳይሆን እግርም ምስክር ነው። ሲራመዱ የመሬቱ ምቾትና እንደ ስፖንጅ ስምጥ ስምጥ ማለት ለምነቱን ይናገራል። በሄልሲንኪ ሴኔት እና ካንሳላስቶሪ አደባባዮች እንደእኛዎቹ አራት እና ስድስት ኪሎ አደባባዮች ናቸው። ቤተ-መንግስት፣ ዩኒቨርሲቲ፣ ፓርላማ፣ ቤተ-መጽሐፍት እና ቤተክርስቲያንን አጎራብተው ይዘዋል። የሄልሲንኪ ሕንጻዎች እንደ ሌሎች የአውሮፓ አገራት ውብና የሥነ-ሕንጻ ጥበብ የሚታይባቸው ናቸው። የነዋሪዎች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ ከተማዋ አልተጨናነቀችም። በአስፋልትና ደረጃውን በጠበቀ ኮብልስቶን የተሰራው የከተማዋ አውራ ጎዳና ከዘመናዊ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ የህዝብ አውቶቡስና የኤሌክትሪክ ባቡር ያስተናግዳል። ለአውሮፓ ከተሞች አዲስ የሆነ ሰው ኮብልስቶኑ የእግረኛ መንገድ መስሎት መሐል የመኪና መንገድ ላይ ሊገኝ ይችላል። እኔም የተረፍሁት እንዲህ አይነቱን የመኪና መንገድ በአንድ ወቅት በኢጣልያ በማየቴ ነበር። የተፈጥሮ ውበት ደምቆ የሚታይባት ፊልናልድ ሲልቨር በርች የተሰኘው ብርማ ቀለም ቅርፊት ያለው ዛፍ እና ቡናማ ድብ ብሔራዊ መለያዎቿ ናቸው። በረጃጅሞቹ ዛፎች መሐል ከእንስሳት ባሻገር ስትሮበሪና እንጉዳይን ጨምሮ ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ዕጽዋት ይገኛሉ። በፊንላንድ ብዙ አይነት የእንጆሪ/ስትሮበሪ ዝርያ አለ። ወቅቱ ፍሬ የሚደርስበት አልነበረም እንጂ ከጫካዎቹ መሐል ገብቶ በተለያዩ የስትሮበሪ ፍሬዎች ቅርጫት ሞልቶ መውጣት የተለመደ መሆኑን ተረድቻለሁ። ፊንላንድ የሺህ ሀይቆች ምድር ተብላም ትሞካሻለች። ለቁጥር የሚያዳግቱ በበርካታ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሀይቆችና የውሀ አካላት ከተፈጥሮ ሀብቶቿ መካከል ናቸው። ለጉብኝት በሄድኩባቸው አካባቢዎች ሁሉ የሚቀርብልኝን ኩልል ያለ ንጹህ የመጠጥ ውሃ በፍቅር ነበር የምጠጣው። ግዴታ ካልሆነ የፋብሪካ ውሃ በፊንላንድ ቦታ የለውም። ንጹህ የተፈጥሮ የምንጭ ውሃ ከቧንቧ ይቀዳል። ጽድት ከማለቱ ጣዕሙ። ፊኒሾች ለባህልና ቅርስ ትልቅ ቦታ አላቸው። በተለይ ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ቁርኝት አስገራሚ ነው። በአብዛኛው አፍሪካ ውስጥ የሚነገር አፈ-ታሪክና ተረት በፊንላንድም ከተፈጥሮ በተለይም ከዛፎችና ከእንስሳት ጋር ተያይዞ ሲተረትና የመድረሻቸው መነሻ እንደሆነ ሲነገር ተደንቄያለሁ። በጉብኝታችን በአንዱ ቀን ኑኪሲኦ ብሔራዊ ፓርክ ሄድን። ይህ ደግሞ እጅግ የተለየ ተፈጥሮን ማያ ስፍራ ነው። በረዣዥም ዛፎች መሐል ካደረግነው ጉዞ በኋላ የቀረበልን ባህላዊው የፊንላንድ የሳውና እና የዋና ግብዣ ነበር። ሳውና የፊንላንድ ባህል ነው። በእንግሊዝኛ ቋንቋ መዝገበ ቃላት ውስጥ ያለ የፊኒሽ ቃል “ሳውና” እንደሆነ ይነገራል። ዛሬ በዓለም ላይ በተለይም በባለኮከብ ሆቴሎች በስፋት የምናገኘው ሳውና መነሻው ፊንላንድ ናት። በርካታ የሳውና ስፍራዎች ከመኖራቸው የተነሳ የሳውና ቁጥር በአገሪቱ ከተመዘገቡ መኪኖች ቁጥር ይበልጣል ይባላል። ግብዣውን ሁላችንም በደስታ ነበር የተቀበልነው። በባህሉ መሰረት ሳውና ውስጥ በቅጠል እየተጠበጠብን ከፍተኛ ሙቀት ሲሰማን ከፊት ለፊት ባለው ቀዝቃዛ የተፈጥሮ ሀይቅ ውስጥ በመግባት ዋና የሚችል ዋኝቶ የማይችል ደግሞ በመነከር ሰውነቱን አቀዝቅዞ እንደገና ወደሳውናው ይመለሳል። የተለየ ነው።     የጉብኝቱ ዋና አስተባባሪ አና ላሚላ ትባላለች። የ35 ዓመት የስራ ልምድ ያላት ብስል ዲፕሎማት ናት። በተለያዩ አገራት ፊንላንድን ወክላ ሰርታለች። አሁንም በአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አምባሳደር ነች። ትክክለኛ የኮሙኒኬሽን ሰው ናት። አንቺ ያልኳት በአንቱታ ላርቃት ባለመፈለጌ ነው። ለነገሩ ስትታይም የ35 ዓመት ወጣት እንጂ የ35 ዓመት የስራ ልምድ ያላት አትመስልም። አንድ ቀን አን “መኮንን” በሚለው የአያቴ ስም እየጠራችኝ ስምሽ እኮ የፊኒሽ/የፊንላንድ ነው ይህን ታውቂያለሽ? ከእኛ ጋር ዝምድና ይኖርሽ ይሆን?" አለችኝ ፈገግ ብላ። "ኸረ በፍፁም ኢትዮጵያዊት ነኝ" አልኳት። ትክክል ነበረች። አጭር የፅሁፍ መልዕክት የመለዋወጥ ሀሳብን ለመጀመሪያ ጊዜ ለዓለም ያስተዋወቀው “ማቲ መኮንን” የተባለ ፊንላንዳዊ ኢንጂኒየር ነው። የቴክኖሎጂ ነገር ከተነሳ አብዛኞቻችን ከተንቀሳቃሽ ስልክ ጋር ስንተዋወቅ የያዝነው ኖኪያ የፊንላንድ ምርት ነው። የመኮንንን ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ በተንቀሳቃሽ ስልክ አማካኝነት ለዓለም ይፋ ያደረገውም ኖኪያ ነው። አሁንም ኖኪያ በኔትወርክ ዝርጋታ ጭምር እየሰራ ያለ ግዙፍ የቴሌኮም ተቋም ነው። ኢትዮጵያና ፊንላንድ የረዥም ዓመታት የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው። ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸው 66 ዓመታትን ተሻግሯል። ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ከእርዳታና ትብብር ባሻገር በተለያየ መስክ በጋራ ትሰራለች። በጉብኝቴ ወቅት ያገኘኋቸው የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሌና ቫልቶነን ይህን ግንኙነት የማሳደግ ፍላጎት መኖሩን ነግረውኛል። ከንግድና ኢንቨስትመንት በተጨማሪ ኖኪያን ከመሰሉ ኩባንያዎች ጋር የሚደረግ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና በአገሪቱ ቴክኖሎጂ መዘመኑን የተረዳሁት በአገሪቱ ብሔራዊ የሚዲያ ተቋም ይሌ ያለማንም እርዳታ ዜና ቀርጾ የሚያሰራጭ ሰው አልባ ሮቦትድ የስቱዲዮ ቴክኖሎጂ ስመለከት ነበር። ፊንላንድ በትምሕርት ጥራትም ስሟ በቀዳሚነት ይነሳል። በአገሪቱ ከ800 በላይ፤ በመዲናዋ ደግሞ 40 የሚጠጉ ቤተ-መጻሕፍት አሉ። ከአገሪቱ ፓርላማ አቅራቢያ የሚገኘውና አገሬው የእኩልነት ተምሳሌት ነው የሚለው የሄልሲንኪ ግዙፉ ማዕከላዊ ቤተ-መጽሐፍት ኦዲ ይባላል። በውስጡ በርካታ አገልግሎቶችን ይዟል። ንባብ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ የባህልና ፈጠራ ታለንቶችን ያስተናግዳል። ከልጅ እስከ አዋቂ ለሁሉም ቦታ አለው።   ፊንላንድ ዜጎቿ በደስታ ግብር የሚከፍሉባት አገር መሆኗን የአገሪቱ የታክስ አስተዳደር ሲናገር በኩራት ነው። ግብር መሰወር፤ ክፈሉ ብሎ በየግዜው መቀስቀስን የመሳሰሉ ነገሮች እዛ ቦታ የላቸውም። የኩባንያም ሆነ የግለሰብ ግብር ከፋዮች በታማኝነት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በወቅቱ እንደሚወጡ አስተዳደሩ ይገልጻል። ይህም የዜጎች ፍላጎትን ለማሟላት በተሰራ ስራ የተፈጠረ መሆኑን የተመለከትኳቸው ተቋማት ሃላፊዎች ይገልጻሉ። ዜጎች በመንግስት ላይ ከፍተኛ እምነት አላቸው። በፊንላንድ የዜጎች ደስተኝነት የሰላምና ነጻነት መገለጫ እንደሆነ ምሁራኖቻቸው በጥናት ስራዎቻቸው ጭምር ይመሰክራሉ። የደስታቸው ምንጭ ነጻና ጥራት ያለው ትምሕርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፤ በፍትህና እኩልነት፤ በበጎ አድራጎት ተግባር፤ የእናቶችና ህጻናት ጤናን ጨምሮ አርአያ የሚሆኑ ጠንካራ የማሕበራዊ ደህንነትና ትስስር ስራዎች የመጡ ውጤቶች እንደሆኑ ይገለጻሉ። በጾታ እኩልነት ሴቶች በሁሉም መስክ ጥሩ ስፍራ አላቸው። በፖለቲካውም ከወንዶች ተቀራራቢ ቦታ እንዳላቸው የአገሪቱን ፓርላማ ስንጎበኝ ተረድቻለሁ። ከ200 የምክር ቤት አባላት 91ዱ ሴቶች ናቸው። የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ፊንላንድ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደስተኛ አገራት ደረጃ ላይ ለስምንት ተከታታይ ዓመታት የከፍታ ስፍራዋን ሳትለቅ በቁጥር አንድ ላይ እንድትቆይ አድርጓታል። ዜጎቿ በቀጣዩ ዓመትም ለዘጠነኛ ጊዜ የዓለም የደስተኞች አገር ሆና ትቀጥላለች የሚል እምነት አላቸው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም