ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የሀገራችንን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረውን ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የትግበራ ምዕራፍ ዛሬ በይፋ አስጀምረናል-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Dec 20, 2025 0
ኢትዮጵያ የጀመረችውን ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ምርጫ ሳይሆን ግዴታችን ነው። ላለፉት አምስት ዓመታት ስንተገብረው የቆየነው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ሀገራችንን በቴክኖሎጂ የታገዘ የኢኮኖሚ መሠረት ላይ ለማቆም ያስቻሉ ተጨባጭ ውጤቶችን አስመዝግቧል። ከተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች መካከልም የዲጂታል መሠረተ ልማት፣ የሳይበር ምህዳር ደህንነት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ፣ ዲጂታል ፋይናንስና ክፍያ፣ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ዲጂታል ክህሎት የተላበሰ ብቁ ዜጋ መፍጠር ተጠቃሽ ናቸው።   አዲሱ ስትራቴጂ በተቀናጀ አመራርና በጠንካራ መዋቅር የሚመራ ሀገራዊ ስትራቴጂ ነው። ስትራተጂው ሁሉን አቀፍና አካታች የዲጂታል አገልግሎቶችን ተደራሽ ያደርጋል፤ ዜጎችን ማዕከል ያደረገ ዲጂታል መንግሥት ይገነባል፤ የሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችንና ስታርታፖችን ያበረታታል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት ከተለመደው አካሄድ ወጥተን፣ በፈጠራና በፍጥነት የታጀበ የዲጂታል ዝላይ ጉዞ ማድረግን ይጠይቃል። ለዚህ ደግሞ የመንግሥት ተቋማትና የግሉ ዘርፍ አገልግሎታቸውን ይበልጥ በማዘመን፣ የልማት አጋሮች ድጋፋቸውን ከስትራቴጂያችን ጋር በማጣጣም፣ ወጣቶችና ባለሙያዎች በፈጠራ አቅማቸው ሀገራዊ መፍትሔዎችን በማመንጨት፣ የድርሻቸውን እንዲወጡ አደራ እላለሁ። የኢትዮጵያን ብልፅግና በዲጂታል እውቀትና ፈጠራ እናሳካዋለን። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
በምእራብ ወለጋ ዞን ሠላምን በማስፈን ለህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን እንደግፋለን --ነዋሪዎች
Dec 20, 2025 19
ጊምቢ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፡-በምእራብ ወለጋ ዞን ሠላምን በማስፈን ለህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን እንደግፋለን ሲሉ በጊምቢ ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ውይይት ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ገለጹ። ''የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ በዞኑ ከተለያዩ ወረዳዎች የተወጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ህዝባዊ ውይይት በጊምቢ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ የተሳተፉ የዞኑ ነዋሪዎች በዞኑ ሠላምን በማስፈን ረገድ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝቡን ጥያቄ የመለሱ ናቸው ብለዋል። ከለውጡ ዓመታት ወዲህ በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን አንስተዋል። በተለይም በህዝቡ ዘንድ የመልካም አስተዳዳር ችግር ሆነው የቆዩ መሰረተ ልማቶች ተቋማት ግንባታም በፍጥነት እየተከናወነ በመሆኑ መንግስትን አመስግነዋል። በቀጣይም ሠላምን በማስፈን ለህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን እንደግፋለን ሲሉ ተናግረዋል። ይሁን እንጂ አሁንም አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮች እልባት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ጠቁመው የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ እንዲፋጠን ጠይቀዋል። በተጨማሪም ህገ -ወጥ ንግድን ጨምሮ የኑሮ ውድነትን የሚያባብሱ ተግባራትን የመቆጣጠር ስራ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ሀላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ፣ የለወጡ መንግስት የህዝቡን ሁሉንተናዊ ህይወት ለማሻሻል እየተጋ ይገኛል ብለዋል። በተለይም በምዕራብ ኦሮሚያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ ህዝቡ ትኩረቱን ልማት ላይ እንዲያደርግ ማስቻሉን ገልጸው የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታም በስፋት መከናወኑን አንስተዋል። መንግስት የህዝቡን የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች የሚጠናከሩ ሲሆን የኑሮ ውድነትን ለመቀነስም ሰፋፊ እንቅስቃሴዎች ይደረጋሉ ብለዋል።   የምዕራብ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ በበኩላቸው በዞኑ ሰላምን በማፅናት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች ቀጥለዋል ብለዋል። በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎችን ማጠናከር እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቀነስ ዋና የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል።      
ፍልሰት በአግባቡ ካልተመራ በዜጎችና ሀገር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያስከትላል
Dec 20, 2025 18
ወላይታ ሶዶ፤ታሕሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ፍልሰት በአግባቡ ካልተመራ በዜጎችና ሀገር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያስከትል ተገልጿል። በመሆኑም ፍልሰትን ወጥ በሆነ መንገድ በአግባቡ ለማስተዳደር የሁሉም ባለደርሻ አካላት ርብርብ ያስፈልጋል ተብሏል። "የዜጎች ፍልሰትን ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ኮንፈረንስ ዛሬ በሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። በኮንፍረንሱ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፈሰር ክንደያ ገብረህይወት በመድረኩ እንዳሉት፤ ፍልሰት በአግባቡ ካልተመራ በዜጎችና ሀገር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያስከትላል። ሆኖም በአግባቡ ማስተዳደር ከተቻለ የዜጎችንና የሀገርን ኢኮኖሚ ለመገንባት ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። ፍልሰትን በአግባቡ ለማስተዳደር የሁሉም ባለደርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥናትና ምርምር በማድረግ ፍልሰትን ወጥ በሆነ መንገድ ማስተዳደር ለሚያስችል ፖሊሲ ግብአት ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው አንስተዋል። ፍልሰትን በአግባቡ ማስተዳደር የሚያስችል በምርምር የታገዘ ስርዓት እንዲበጅ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚናን ለማጎልበት ሚኒስቴሩ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ፍልሰትን በምርምርና ጥናት በማገዝ ለዘላቂ ልማት ለማዋል ከአርባምንጭ፣ ዲላ እና ጂንካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር አብረው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በሀገሪቱ የግብርና፣ የማዕድን፣ ኢንዱስትሪና የቱሪዝም ልማት አካታችና ትርጉም ባለው መንገድ ለዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ካሠች ኤልያስ፤ ፍልሰትን ለዘላቂ ልማት ለማዋል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተጀመረው ጥረት የዘርፉን ችግር ለማቃለል አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። ህገ-ወጥ ፍልሰትን ለማስቆም ቢሮው ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በኮንፈረንሱ ላይ በፍልሰት ዙሪያ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ አስጀመሩ 
Dec 20, 2025 25
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ):- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ዛሬ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ መጀመሩን ጠቁመው፤ ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል።   ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በኢሉአባቦር ዞን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ድሎች እንዲቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን --ነዋሪዎች
Dec 20, 2025 22
መቱ ፤ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ድሎች እንዲቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ በመቱ ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ውይይት ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ገለጹ። ''የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ከመቱ ከተማና ከኢሉአባቦር ዞን ወረዳዎች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮችን ያሳተፈ ህዝባዊ ውይይት በመቱ ከተማ ተካሄዷል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የዞኑን ህዝብ ተጠቃሚ ያደረጉ ታላላቅ የልማት ውጤቶች መመዝገብ ችለዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የመቱ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ሼህ ኤልያስ ሙሐመድ፣ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ልማቶች በሁሉም መስክ እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። ዘመናዊ የአሰራር ዘዴን በመከተል የግብርና ልማት በመተግበሩ ትልቅ ውጤት እየተመዘገበ የሕዝብን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላው ሊቀ ስዩማን ቀሲስ ታከለ ዳዲ በበኩላቸው መንግስት አንድነትን በማጽናት ልማትን ለማስፋፋት የሚያከናውነው ስራ የሚደገፍ ነው ብለዋል። በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ድሎች እንዲቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ ተናግረዋል። አቶ ደበላ ዶርፎ በበኩላቸው በለውጡ ዓመታት መንግስት በሰላም፣ በልማት፣ በዲፕሎማሲ እና በሌሎች መስኮች ያሳየው ቁርጠኝነትና የተመዘገቡ ውጤቶች የሚያስመሰግኑ ናቸው ብለዋል። ሆኖም የዞኑንና የከተማውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችሉና ትኩረት የሚያሻቸው አንዳንድ ጉዳዮች አንዳሉም ተሳታፊዎቹ አንስተዋል። ከነዚህም መካከል የኖሌ- አልጌ- መቱ እንዲሁም የበቾ-ሳይለም-አጋሮ አስፋልት መንገዶች ግንባታ መጓተት፣ የአባቦር ስታዲየምና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ልማትን መፋጠን እንዳለባቸው ጠይቀዋል። የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት ሕዝቡ ከልማቱ ተጠቃሚ እንዳይሆን ትልቅ ተግዳሮት በመሆኑ መፍትሔ የሚሻ መሆኑንም አንስተዋል። በሌላ በኩል በዞኑ እየተተገበሩ የሚገኙ የሻይ እና የሩዝ ልማት ስራዎችን ተከትሎ የማቀነባበሪያ ፋብሪካ ሊታሰብበት ይገባል ሲሉም አንስተዋል። በዞኑ የሚገኘው ትልቅ የሀገር ሀብትና የቱሪዝም አቅም መሆን የሚችለው የሶር ፏፏቴ ስፍራ ልማት ትኩረት እንዲደረግበትም አክለዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ሻፊ ሁሴን፣ መንግስት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎችን በትኩረት እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ሕብረተሰቡም የስራ ባሕሉን ይበልጥ በማሻሻል ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ እንዲተጋ ያሳሰቡት አቶ ሻፊ ዘላቂ ሰላም ለማስፈንም መትጋት ይገባል ነው ያሉት። የኢሉአባቦር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ፣ የሻይ ልማትን ጨምሮ ሌሎች አዳዲስ የግብርና ልማት ኢኒሼቲቮችን ለማስፋፋት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የሚታይ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ አስጀመሩ 
Dec 20, 2025 25
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ):- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ዛሬ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ መጀመሩን ጠቁመው፤ ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል።   ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የክልሉን ሰላም ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ-ርእሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ
Dec 20, 2025 65
ጋምቤላ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል ሰላምን ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ በሁሉም ዘርፎች የጀመርናቸው የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። በክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሰ መስተዳድሯ በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት፥ የጥፋት ተልእኮ ያነገቡ አካላት የክልሉን ሰላም በማናጋት መረጋጋት እንዳይኖር እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ይሁን እንጂ በሰላም ወዳዱ ህዝብና በፀጥታ ሃይሉ ጠንካራ ክትትል ህግ የማስከበር ስራ እየተሰራና አጥፊዎችም በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል። በህግ ማስከበሩ የሀገር መከላከያና ሌሎች የፀጥታ አካላት ላደረጉትና እያደረጉ ላለው የተቀናጀ ስራ አድንቀዋል። የክልሉን ሰላም ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን በማስቀጠል ረገድ የክልሉ መንግስት በቁርጠኝነት የሚሰራ መሆኑን አረጋግጠው፥ የህዝቡም እገዛና ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርእሰ መስተዳድሯ ጥሪ አቅርበዋል።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የሁሉም የላቀ ተሳትፎና ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል። አጠቃላይ ህብረተሰቡ በተለይም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ጥፋትን ማውገዝና ስለ ሰላም ማስተማር እንዳለባቸው ተናግረዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሙላቱ ጀልዱ፤ ሰራዊቱ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የሀገርን ሰላም የማስጠበቅና ህግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   ለጥፋት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎችም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ለልማት ስራዎች መሳካት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።  
የኢትዮ-ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትብብር የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያፋጥን የደቡብ ደቡብ ትብብር ወሳኝ መገለጫ ነው
Dec 20, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያና ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትብብር የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያፋጥን የ"ደቡብ-ደቡብ ትብብር" ወሳኝ መገለጫ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። የኢትዮጵያና ሕንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምርና ትምህርትን ትብብር ለማሳደግ ያለመ መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።   መርሃ-ግብሩም በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎችና በሕንድ ስመ-ጥር የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ትብብር በአምስት ዓመታት ውስጥ 1ሺ 200 የድህረ-ምረቃ(ፒኤችዲ) ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎችን ለማሰልጠን ዓላማ አድርጓል። በመርሃ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ፤ ኢትዮጵያና ሕንድ መካከል ረጅም ዘመናትን የተሻገረ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው ብለዋል። የኢትዮ-ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የትብብር መርሃ ግብርም በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ የሰው ሃብት በመፍጠር የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል። በትብብር መርሃ ግብሩ የተካተቱ ስምንት የሕንድ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶችም ችግር ፈቺ የምርምርና ፈጠራ ሥራዎችን በማካሄድ የደቡብ ደቡብ ትብብርን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በቅርቡ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝትም የሀገራቱን ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማሸጋገር እንዳስቻለ አስረድተዋል።   የኢትዮ-ሕንድ የጋራ የድህረ-ምረቃ ትምህርት አስተባባሪ ፕሮፌሰር ክሪሽና ራጅ፤ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውህሎትና በቴክኖሎጂ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ነው ብለዋል። በኢትጵያና ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል የተፈጠረው የትብብር አጋርነትም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ወሳኝ ሚና እንደሚጫዎት ገልጸዋል። ኢትዮ-ሕንድ የትምህርት የትብብር መርሃ-ግብር ማስጀመሪያ የተገኙት የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ታደሰ ረጋሳ (ዶ/ር)፤ መርሃ ግብሩ የሀገራቱን የትምህርት ትብብር ዘላቂ አጋርነትን ያረጋግጣል ብለዋል። የኢትዮ-ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትብብር የሰው ሃብት ልማት አቅምን ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ያሉት ደግሞ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) ናቸው። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የሀገራቱ የምርምርና ትምህርት ተቋማት ትብብር የድህረ-ምረቃ ተማሪዎችን የምርምር ውጤት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያሳድጋል ብለዋል። መርሃ-ግብሩ ኢትዮጵያ ለጀመረችው የኢኮኖሚና የማህበራዊ ዕድገት የሚመጥን ብቁ የሰው ሃይል ለማፍራት በምታደርገው ጥረት ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረውም ተገልጿል።
የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብርን ያጎለበተ ነው
Dec 20, 2025 60
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ክብር ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ያጎለበተ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኑነት ፖሊሲ ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን እያሳለጠ መሆኑንም ገልጸዋል። ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር፣ እኩልነትና የጋራ ተጠቃሚነት፣ በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባትና ለዓለም አቀፍ ስምምነቶች መገዛት የሚሉት አንድ ሀገር በውጭ ግንኙነት የሚከተላቸው ዋና ዋና መርሆች ናቸው። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትም ከትናንት እስከዛሬ ከራስ ብሔራዊ ጥቅም የሚቀዳ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተመሰረተ የኢኮኖሚና ቅድሚያ ለጎረቤት ዲፕሎማሲያዊ ትብብርን እያጎለበተ ይገኛል። ይህም የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ ገናና የሥልጣኔ ታሪክ ከአሁናዊ ዓለም ጋር በማሰናሰል ከብሔራዊ ክብርና ፍላጎት የተወዳጀ ፍሬያማ የዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትን በማጎልበት ወርቃማ ዕድል ሆኖ እያገለገለ ነው። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የዜጎችን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተደማጭነትና ልዕልና ለማስከበር አዎንታዊ ተፅዕኖ አላቸው ብለዋል። የመደመር እሳቤም የዜጎችን አንድነት በማስጠበቅ የኢትያጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ክብር ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ያጎለበተ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግስት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲና ቅድሚያ ለጎረቤት የሚሉት ወሳኝ መርሆች መሆናቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲም የውጭ ኢንቨስትመንትና የንግድ ትብብርን በማሳደግ የጋራ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ የትብብር መርህ መሰረት መሆኑን የአውሮፓ ሕብረትን በአብነት ጠቅሰዋል።   በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የስልጠና ክፍል ዳይሬክተር ጀነራል መላኩ ሙሉዓለም፤ ኢትዮጵያ በትብብርና አብሮ ማደግ ላይ የተመሰረተና በረጅም ታሪክ የዳበረ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ያላት ሀገር ናት ብለዋል። ኢትዮጵያ የብሪክስ (BRICS+) አባልነትን መቀላቀሏም የአፍሪካን ድምጽ በዓለም አቀፍ መድረኮች ለማንጸባረቅ የሚረዳ ወሳኝ የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በሰጥቶ መቀበል መርህ የዳበረውን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር በተሻለ የዕድገት ምዕራፍ ለማሳደግ እንደሚሰራ አስረድተዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት የዜጎችን የአገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል-ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ
Dec 20, 2025 79
ጅግጅጋ፤ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት የዜጎችን የአገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት የሚደረግ መሆኑን የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ገለጹ። በሶማሌ ክልል የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የተጀመረ ሲሆን በማስጀመሪያ መርሐግብር ላይ ሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ እንዲሁም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ እና ሌሎች የፌዴራል የክልሉ መንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ዛሬ አገልግሎት የጀመረው የጅግጅጋ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት በማስቀረት ፈጣን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል በመሆኑ ተጠያቂነትን ለማስፈንም እንደሚረዳ ተናግረዋል። ማዕከሉ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል ዘመናዊ መሰረተ ልማት እና የሰው ሀይል የተሟላለት መሆኑንም አንስዋል። አገልግሎቱን ለማስፋፋትም በቀጣይ በክልሉ 13 ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተግባራዊ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።   በመሆኑም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በሌሎች ከተሞችም በማስፋት የዜጎችን የአገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ በበኩላቸው፥ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ፣ ከአድሎ የጸዳ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።   የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ መንግሥትና ህዝብን የበለጠ የሚያቀራርብ እንዲሁም ሰው ተኮር የአገልግሎት ልህቀትን ለማረጋገጥም የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል። በአጠቃላይ ማዕከሉ መንግስት በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ የጀመረው ሪፎርም ለማሳካት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑንም አብራርተዋል። ዛሬ አገልግሎት የጀመረው ማዕከሉ 9 ተቋማትን በውስጡ የያዘ ሲሆን 32 አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተገልጿል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በክልሉ ዘላቂ ሰላምንና ልማትን ለማረጋገጥ ተሳትፏችንን እናጠናክራለን - ወጣቶች
Dec 20, 2025 53
ደብረብርሃን፤ ታሕሳስ 11/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ በሚደረገው እንቅስቃሴ ወስጥ ተሳትፏቸውን በማጠናከር የድርሻቸውን እንደሚወጡ የደብረብርሃን ከተማ ወጣቶች ገለጹ። "ለዘላቂ ሰላምና ልማት የወጣቶች ሚና " በሚል መሪ ሀሳብ የክልሉና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ከከተማው ወጣቶች ጋር ተወያይተዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች ውስጥ ወጣት ዓሊ ሀሰን፣ ወጣት አንዱ ዓለም ጌታቸው እና ወጣት ወንድዬ ዘገየ በሰጡት አስተያየት፤በከተማው የተጀመሩ የልማት ስራዎች የወጣቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በመሆኑ ይህንን በማስቀጠል ሰላም በዘላቂነት ለማስከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። የሀሰት ወሬን በማጋለጥ በሰላም ግንባታ ላይ አተኩረው በመስራት ልማትን ለማፋጠን ተሳትፏቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። የተጀመሩ ፕሮጀክቶች የበለጠ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሚናቸውን እንደሚወጡም አንስተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአማራ ክልል የማሕበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በክልሉ ዘላቂ ሰላም ሰፍኖ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማስቀጠል እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ ውስጥ የወጣቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ነው። ወጣቶች ሀገር ተረካቢና ትውልድ አስቀጣይ እንደመሆናቸው ይህንን በመጠበቅ ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማፋጠን ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል ⵆ ከባሕላዊ እሴቶች ካፈነገጡ የማህበራዊ ሚዲያ ፣ ከባዳና ባንዳዎች እኩይ እሳቤ እራሳቸውን በማራቅ ለሀገር ሰላምና ብለፅግና የድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸዋም አንስተዋል። በየዘርፉ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋጋጥ መንግስት አበክሮ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የክልሉ ሴቶች ፣ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ዘላለም አረጋ፤ ወጣቶች የጀመሯቸው የልማት ስራዎችን በማጠናከር የአካባቢን ፀጋ ለመጠቀም የሚያስችል እይታን ማስፋት አለባቸው ብለዋል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፤ የወጣቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ በወጣቶች ለተነሱት ጥያቄዎችና ጥቆማዎች በቀጣይ እየታየ ምላሽ በመስጠት እንደሚስተካከሉ አረጋግጠዋል። በመድረኩ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ከደብረ ብርሃን ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ወጣቶች ተሳትፈዋል።      
የክልሉን ሰላም ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ-ርእሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ
Dec 20, 2025 65
ጋምቤላ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል ሰላምን ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ በሁሉም ዘርፎች የጀመርናቸው የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። በክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሰ መስተዳድሯ በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት፥ የጥፋት ተልእኮ ያነገቡ አካላት የክልሉን ሰላም በማናጋት መረጋጋት እንዳይኖር እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ይሁን እንጂ በሰላም ወዳዱ ህዝብና በፀጥታ ሃይሉ ጠንካራ ክትትል ህግ የማስከበር ስራ እየተሰራና አጥፊዎችም በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል። በህግ ማስከበሩ የሀገር መከላከያና ሌሎች የፀጥታ አካላት ላደረጉትና እያደረጉ ላለው የተቀናጀ ስራ አድንቀዋል። የክልሉን ሰላም ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን በማስቀጠል ረገድ የክልሉ መንግስት በቁርጠኝነት የሚሰራ መሆኑን አረጋግጠው፥ የህዝቡም እገዛና ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርእሰ መስተዳድሯ ጥሪ አቅርበዋል።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የሁሉም የላቀ ተሳትፎና ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል። አጠቃላይ ህብረተሰቡ በተለይም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ጥፋትን ማውገዝና ስለ ሰላም ማስተማር እንዳለባቸው ተናግረዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሙላቱ ጀልዱ፤ ሰራዊቱ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የሀገርን ሰላም የማስጠበቅና ህግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   ለጥፋት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎችም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ለልማት ስራዎች መሳካት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።  
ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ማካሄድ የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ ነው - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Dec 20, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ማካሄድ የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በተለያዩ አካባቢዎች የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከየካቲት 16/2014 ዓ.ም ጀምሮ በተለያየ ምዕራፍ አጀንዳ በማሰባሰብ ሂደቱ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ ተሸጋግሯል ብለዋል። በዚህም በአስራ አንድ ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ ተሳታፊዎችን የመለየትና አጀንዳ የማሰባሰብ ስኬታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም የህብረተሰቡን ፍላጎት በማካተት በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን የማደራጀትና ግብዓቶችን የማሰባሰብ ሥራ በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ግልጸኝነት፣ አካታችና ገለልተኝነት ለማስጠበቅም ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምሁራን፣ ሲቪል ማኅበራትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠቱን አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ግልጸኝነትና አካታችነት ምኅዳር ለማስጠበቅም በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጋር አጀንዳ ማሰባሰብና ተወካዮችን ማስመረጥ ያስቻለ ስኬታማ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል። በውጭ የሚኖሩ ዜጎች አጀንዳቸውን በማስረከብ ተወካዮቻቸውን የማስመረጥ ሥራም ተሰርቷል ብለዋል። በትግራይ ክልልም ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ምሁራን ጋር በሀገራዊ ምክክር ጉዳዮች ላይ በተለያዩ ጊዜያት ጥልቅ ውይይቶች መካሄዳቸውን አንስተዋል። በቀጣይም ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምሁራን፣ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በማወያየት አጀንዳ የማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ ሥራ እንደሚከናወን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በዋና ዋና ሀገራዊ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ምክክር በማካሄድ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በማለም እየሰራ ይገኛል።
የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብርን ያጎለበተ ነው
Dec 20, 2025 60
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ክብር ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ያጎለበተ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኑነት ፖሊሲ ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን እያሳለጠ መሆኑንም ገልጸዋል። ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር፣ እኩልነትና የጋራ ተጠቃሚነት፣ በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባትና ለዓለም አቀፍ ስምምነቶች መገዛት የሚሉት አንድ ሀገር በውጭ ግንኙነት የሚከተላቸው ዋና ዋና መርሆች ናቸው። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትም ከትናንት እስከዛሬ ከራስ ብሔራዊ ጥቅም የሚቀዳ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተመሰረተ የኢኮኖሚና ቅድሚያ ለጎረቤት ዲፕሎማሲያዊ ትብብርን እያጎለበተ ይገኛል። ይህም የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ ገናና የሥልጣኔ ታሪክ ከአሁናዊ ዓለም ጋር በማሰናሰል ከብሔራዊ ክብርና ፍላጎት የተወዳጀ ፍሬያማ የዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትን በማጎልበት ወርቃማ ዕድል ሆኖ እያገለገለ ነው። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የዜጎችን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተደማጭነትና ልዕልና ለማስከበር አዎንታዊ ተፅዕኖ አላቸው ብለዋል። የመደመር እሳቤም የዜጎችን አንድነት በማስጠበቅ የኢትያጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ክብር ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ያጎለበተ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግስት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲና ቅድሚያ ለጎረቤት የሚሉት ወሳኝ መርሆች መሆናቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲም የውጭ ኢንቨስትመንትና የንግድ ትብብርን በማሳደግ የጋራ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ የትብብር መርህ መሰረት መሆኑን የአውሮፓ ሕብረትን በአብነት ጠቅሰዋል።   በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የስልጠና ክፍል ዳይሬክተር ጀነራል መላኩ ሙሉዓለም፤ ኢትዮጵያ በትብብርና አብሮ ማደግ ላይ የተመሰረተና በረጅም ታሪክ የዳበረ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ያላት ሀገር ናት ብለዋል። ኢትዮጵያ የብሪክስ (BRICS+) አባልነትን መቀላቀሏም የአፍሪካን ድምጽ በዓለም አቀፍ መድረኮች ለማንጸባረቅ የሚረዳ ወሳኝ የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በሰጥቶ መቀበል መርህ የዳበረውን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር በተሻለ የዕድገት ምዕራፍ ለማሳደግ እንደሚሰራ አስረድተዋል።
ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራዊ ምክክሩን እድል ልንጠቀምበት ይገባል-የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Dec 20, 2025 70
ሀዋሳ፤ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ) ፡-የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራዊ ምክክሩን እድል ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉ በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አካታችና አሳታፊ የሆነ ምክክር በማድረግ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር ይቻል ዘንድ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። በእስካሁኑ ሂደትም የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን በማገባደድ ወደ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ለመሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የምክክር ሂደቱንና አጠቃላይ የሚኖረውን ፋይዳ በተመለከተ ኢዜአ በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራርና አባላትን አነጋግሯል። የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊና የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ በለጠ ሲጌቦ፤ በዓለም ላይ የተለያዩ ሀገራት በምክክር ከመበተን ወደ አንድነት በመምጣት ዘላቂ ሠላም ማረጋገጥ መቻላቸውን አንስተዋል። በመሆኑም በኢትዮጵያ በሂደት ላይ ያለው ምክክር ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ከግጭት ለመውጣት ከምክክር የተሻለ እድልና አማራጭ የለም ሲሉም ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር በመሆኑ በአጀንዳ ላይ ተመካክሮ በመግባባት ችግሮችን በዘላቂነት መፍታትና ብሔራዊ መግባባት መፍጠር የሁላችንም ግዴታ ነው ሲሉ አንስተዋል። እንደ ፖለቲካ ፓርቲ አጀንዳችንን ለኮሚሽኑ ማቅረብ ችለናል ያሉት አቶ በለጠ፥ በምክክሩ በንቃት በመሳተፍ ለስኬታማነቱ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ዋና ሊቀመንበርና የጋራ ምክር ቤቱ አባል አቶ ለገሰ ላንቃሞ፤ የምክክር ሂደት የግጭትና ጦርነት ምክንያቶችን በመግባባት መቋጨት የሚያስችል ቁልፍ መፍትሄ በመሆኑ በትኩረት እየተሳተፍን እንገኛለን ብለዋል። ከመነሻው ጀምሮ በተሳታፊ ልየታም ሆነ በአጀንዳ ማሰባሰብ መድረኮች ላይ የፓርቲያቸው ተሳትፎ መኖሩን አንስተው፥ ለምክክሩ ሂደት ውጤታማነት እስከመጨረሻው እንሰራለን ሲሉም ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባሕል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ እና የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ኤርሚያስ፥ የፖለቲካ ስብራቶችን በማከም በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ፅኑ መሠረት እንዲኖረው መንግስት አበክሮ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፥ እየተንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በመፍታት ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መመካከር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ከምክክር ውጭ የሚደረግ የሃይልና የጥፋት እንቅስቃሴ አንዳችም መፍትሄ የማያመጣ በመሆኑ ይህንን እድል ልንጠቀምበት ይገባል ብለዋል። የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት መመካከር ወሳኝ መሆኑን አንስተው፥ በአጀንዳዎቻችን ላይ በመምከር ለሀገርና ለትውልድ የሚበጅ ታሪክ እንስራ ሲሉ ተናግረዋል።
የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር በመሆን የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል-የቀድሞ ታጣቂዎች
Dec 20, 2025 79
ባሕርዳር፤ታሕሳስ 11/2018(ኢዜአ)፡-የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር በመሆን የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተን መጥተናል ሲሉ በአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ትጥቅ ይዘው ይንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ በመቀበል የተሀድሶ ስልጠና እየወሰዱ ወደ ማሕበረሰቡ መቀላቀላቸውን እንደቀጠሉ ነው። በዚህም መሰረት በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ፋግታ ላኮማ ወረዳ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በፈፀምነው ስሕተትና ባጠፋነው ጊዜ በመጸጸት ወደ ሰላማዊ ሕይወት ተመልሰናል ብለዋል። በሕዝብ ስም እየተማለ አምቡላንስን ማቃጠል፣ መሰረተ ልማቶችን ማውደም፣ ትምሕርት ቤቶች እንዲዘጉ ማድረግና ዘረፋ መፈፀም በቀጥታ ሕዝብን መጉዳት በመሆኑ ከጥፋታችን በመውጣት የሰላምን አማራጭ ተቀብለን መጥተናል ሲሉ ተናግረዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል ዘመነ አዲስ እና ገደፋው ሞላ፤ በአብዛኛው በጫካ ሲንቀሳቀስ የነበረው ታጣቂ በተሳሳተ እሳቤ በጥፋት መንገድ ላይ መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል እየገባ መሆኑን ገልጸዋል። በሕዝብ ስም እንታገላለን የሚል ማደናገሪያ ስለነበር ይህንኑ ሃሳብ በመቀበል ጫካ መግባታቸውን አንስተው በተግባር ሲታይ በሕዝብ ላይ ዘረፋ፣ እገታና ግዲያ መፈፀም በመሆኑ ይሕንን ተግባር በመቃወምና ሰላምን በመሻት መጥተናል ብለዋል። በመሆኑም የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር በመሆን የበደልውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተን መጥተናል ሲሉ ተናግረዋል። ሌሎች በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎችም መንግስት ያቀረበውን የሰላም እድል በመጠቀም መጥተው ሰላማዊ ሕይወታቸውን እንዲጀምሩ መክረዋል።   የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሃላፊ ጌታቸው ቢሻው፤ በዞኑ የሰላምን አማራጭ ተቀብለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማሕበረሰቡ እንዲቀላቀሉ እየተደረገ ነው ብለዋል። አሁንም ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት እያስረከቡ መግባታቸውን ቀጥለው እንዳሉ ጠቁመው፥ ይህም የሽፍታው ስብስብ እኩይ ተግባር በመገንዘቡ አብዛኛው የሰላም አማራጭን እየመረጠ ነው ብለዋል። መንግስት በሆደ ሰፊነት አሁንም የሰላም በሩን ክፍት በማድረግ መቀበሉን እንደሚቀጥል አረጋግጠው፥በሰላም የሚገቡትን የተሀድሶ ስልጠና በመስጠት ፍላጎታቸውን መሰረት በማድረግ የስራ እድል የመፍጠር ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። የሰላምን አማራጭ በማይቀበለው የሽፍታው ስብስብ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
በዞኑ የሕግ የበላይነትንና ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሕብረተሰቡን ያሳተፉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Dec 20, 2025 95
ቡሌ ሆራ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ) ፡- በምዕራብ ጉጂ ዞን የህግ የበላይነትንና ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሕብረተሰቡን ያሳተፉ የተቀናጁ ተግባራት ተጠናከረው መቀጠላቸውን የዞኑ አስተዳደርና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡ የጽሕፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ አየለ ደንባ፣ የመንግስትን የሰላም አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች መመለሳቸውን ቀጥለዋል ብለዋል። ወደ ሰላም የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችም የተሃድሶ ስልጠና እየወሰዱ ወደ ሕብረተሰቡ ተቀላቅለው መደበኛ ህይወት እንዲመሩ እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል። በቀጣይም በዞኑ የሕግ የበላይነትንና ሰላምን በዘላቂነት ለማስከበርና ለማፅናት ሕብረተሰቡን ያሳተፉ የተቀናጁ ተግባራት ተጠናከረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል።   የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ምክትል ኢንፔክተር ፈዬራ ኬይረዲን፤ የቀድሞ ታጣቂዎች በየቀኑ ወደ ሰላም መንገድ እየመጡ መሆኑን አንስተዋል። በተሳሳተ መንገድ ችግር ውስጥ ገብተው የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ሰላም እንዲመጡ አባገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሕዝቡ ተከታታይ ጥረት ሲያደርጉ እንደቆዩ አውስተው ፤ ይህም ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን አስረድተዋል። ከዞኑ ነዋሪዎች መካከል አባገዳ ጃርሶ ዱጎ፣ ከዞኑ ሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ከፍሎች ጋር በመሆን ለቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪ ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡ በዚህም በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች ባህልና እሴታቸውን እንዲሁም ቃላቸውን በማክበር እየተመለሱ በመሆኑ በዞኑ ሰላም ሰፍኗል ብለዋል፡፡ ችግርን በውይይት ከመፍታት በስተቀር እርስ በእርስ በመጎዳዳት የሚገኝ ጥቅም፤ የሚመጣ ለውጥም የለም ሲሉ ገልጸዋል፡፡ ወደ ሰላም ከተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል ሊበን ሸጋ በሰጠው አስተያየት፤ የሰላም አማራጭን ተቀብሎ በመመለስ የበደለውን ሕዝብ ለማካስ መዘጋጀቱን ገልጿል። በጫካ የቀሩትም የሰላም መንገድ በመምረጥ ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱም መልዕክት አስተላልፏል።
የሀገራዊ ምክክር ዕድልን መግፋት በምንም መልኩ አዋጭ አይደለም
Dec 19, 2025 154
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 10/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር የተመቻቸውን የጠረጴዛ ዙሪያ ሀገራዊ ምክክር ዕድልን መግፋት በምንም መልኩ አዋጭ አይደለም ሲሉ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ(ኢዜማ) ሥራ አስፈፃሚ አባል ግርማ ሰይፉ ገለጹ። ኢትዮጵያ የገጠሟትን ተግዳሮቶች ተቋቁማ ተዓምራዊ የዕድገት ለውጦችን እያስመዘገበች መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ(ኢዜማ) ሥራ አስፈፃሚ አባል ግርማ ሰይፉ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ቆይታ አድርገዋል። አቶ ግርማ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ እንዲመጣ ምክንያት የሆነው ለዘመናት የቆየው የዜጎች የጭቆና ትግልና የህልውና ጥያቄ ነው። በተለይም ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ የቀድሞው ገዥ ፓርቲ ኢሕአዴግ የራሱንና የአባላቱን ጥቅም ለማስጠበቅ በዜጎች ላይ የፈጠረው ኢ-ፍትሐዊ አስተዳደር፣ ሕዝቡ በአደባባይ እንዲታገልና ለውጥ እንዲመጣ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ግርማ፤ በአሁኑ ወቅት የተፈጠረውን የሀገራዊ ምክክር አውድ በመተው መሳሪያን በማንገብ የሚንቀሳቀሱ አካላት የዕውቀት አልባነት መገለጫ መሆኑን በጽኑ ተችተዋል። ነፃነት ካመጣው የሰለጠነ የምክክር አውድ ባፈነገጠ መልኩ፣ በነፃነት ስም በመሳሪያና በጉልበት መጓዝን የመረጡ ኃይሎች መፈጠራቸው ለሀገር ልማት እንቅፋት መሆኑን ነው የገለጹት። ባለፉት ሰባት ዓመታት ኢትዮጵያ በርካታ የግጭት ሴራዎችን ተቋቁማ ያስመዘገበችው ውጤት አስደናቂ መሆኑንና ተዓምራዊ የዕድገት ለውጦችን እያስመዘገበች ትገኛለች ሲሉ አብራርተዋል። ኢዜማ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጠረጴዛ ዙሪያ በመምከር መፍትሔ ማምጣትን እንደ ቀዳሚ አማራጭ እንደሚቀበል ገልጸውም፤ የትጥቅ ትግልን በመተው በሐሳብ የበላይነት መወያየት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኢዜማ ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የፖሊሲ አማራጭ ይዞ በመቅረብ፣ የአመራር አባላቱና ደጋፊዎቹ ለነቃ ፉክክር ዝግጅት እያደረጉ መሆኑም አስታውቀዋል። በምርጫ ቦርድ ዕውቅናው የተነሳው የቀድሞ ሕወሓት በክልሉ የሚያሳየው እብሪት መሠረተ ቢስና እውቀት አልባነትን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመው፤ የትግራይ ሕዝብ የፌዴራል መንግሥት ውክልናውን የሚያረጋግጥበትን አማራጭ እንዲፈጠርለት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪል ማኅበራት ሊሠሩ እንደሚገባ ተናግረዋል። በአንድ አንድ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ኃይሎችን በተመለከተ ምርጫውን የማደናቀፍ አቅም እንደሌላቸው ነው የገለጹት። የፓርቲያቸው የፖሊሲ አማራጮች ሌላውን የመጫን ፍላጎት እንደሌለው ጠቁመው፤ በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ሕዝብን በማስቀደም ለሀገር የሚጠቅም ውሳኔ ላይ መድረስ የጋራ ኃላፊነት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ፖለቲካ
በክልሉ ዘላቂ ሰላምንና ልማትን ለማረጋገጥ ተሳትፏችንን እናጠናክራለን - ወጣቶች
Dec 20, 2025 53
ደብረብርሃን፤ ታሕሳስ 11/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ በሚደረገው እንቅስቃሴ ወስጥ ተሳትፏቸውን በማጠናከር የድርሻቸውን እንደሚወጡ የደብረብርሃን ከተማ ወጣቶች ገለጹ። "ለዘላቂ ሰላምና ልማት የወጣቶች ሚና " በሚል መሪ ሀሳብ የክልሉና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ከከተማው ወጣቶች ጋር ተወያይተዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች ውስጥ ወጣት ዓሊ ሀሰን፣ ወጣት አንዱ ዓለም ጌታቸው እና ወጣት ወንድዬ ዘገየ በሰጡት አስተያየት፤በከተማው የተጀመሩ የልማት ስራዎች የወጣቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በመሆኑ ይህንን በማስቀጠል ሰላም በዘላቂነት ለማስከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። የሀሰት ወሬን በማጋለጥ በሰላም ግንባታ ላይ አተኩረው በመስራት ልማትን ለማፋጠን ተሳትፏቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። የተጀመሩ ፕሮጀክቶች የበለጠ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሚናቸውን እንደሚወጡም አንስተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአማራ ክልል የማሕበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በክልሉ ዘላቂ ሰላም ሰፍኖ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማስቀጠል እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ ውስጥ የወጣቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ነው። ወጣቶች ሀገር ተረካቢና ትውልድ አስቀጣይ እንደመሆናቸው ይህንን በመጠበቅ ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማፋጠን ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል ⵆ ከባሕላዊ እሴቶች ካፈነገጡ የማህበራዊ ሚዲያ ፣ ከባዳና ባንዳዎች እኩይ እሳቤ እራሳቸውን በማራቅ ለሀገር ሰላምና ብለፅግና የድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸዋም አንስተዋል። በየዘርፉ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋጋጥ መንግስት አበክሮ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የክልሉ ሴቶች ፣ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ዘላለም አረጋ፤ ወጣቶች የጀመሯቸው የልማት ስራዎችን በማጠናከር የአካባቢን ፀጋ ለመጠቀም የሚያስችል እይታን ማስፋት አለባቸው ብለዋል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፤ የወጣቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ በወጣቶች ለተነሱት ጥያቄዎችና ጥቆማዎች በቀጣይ እየታየ ምላሽ በመስጠት እንደሚስተካከሉ አረጋግጠዋል። በመድረኩ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ከደብረ ብርሃን ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ወጣቶች ተሳትፈዋል።      
የክልሉን ሰላም ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ-ርእሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ
Dec 20, 2025 65
ጋምቤላ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል ሰላምን ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ በሁሉም ዘርፎች የጀመርናቸው የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። በክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሰ መስተዳድሯ በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት፥ የጥፋት ተልእኮ ያነገቡ አካላት የክልሉን ሰላም በማናጋት መረጋጋት እንዳይኖር እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ይሁን እንጂ በሰላም ወዳዱ ህዝብና በፀጥታ ሃይሉ ጠንካራ ክትትል ህግ የማስከበር ስራ እየተሰራና አጥፊዎችም በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል። በህግ ማስከበሩ የሀገር መከላከያና ሌሎች የፀጥታ አካላት ላደረጉትና እያደረጉ ላለው የተቀናጀ ስራ አድንቀዋል። የክልሉን ሰላም ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ የሚጥሩ አካላትን እኩይ አላማ በማክሸፍ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን በማስቀጠል ረገድ የክልሉ መንግስት በቁርጠኝነት የሚሰራ መሆኑን አረጋግጠው፥ የህዝቡም እገዛና ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርእሰ መስተዳድሯ ጥሪ አቅርበዋል።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የሁሉም የላቀ ተሳትፎና ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል። አጠቃላይ ህብረተሰቡ በተለይም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ጥፋትን ማውገዝና ስለ ሰላም ማስተማር እንዳለባቸው ተናግረዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሙላቱ ጀልዱ፤ ሰራዊቱ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የሀገርን ሰላም የማስጠበቅና ህግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   ለጥፋት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎችም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ለልማት ስራዎች መሳካት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።  
ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ማካሄድ የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ ነው - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Dec 20, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ማካሄድ የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በተለያዩ አካባቢዎች የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከየካቲት 16/2014 ዓ.ም ጀምሮ በተለያየ ምዕራፍ አጀንዳ በማሰባሰብ ሂደቱ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ ተሸጋግሯል ብለዋል። በዚህም በአስራ አንድ ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ ተሳታፊዎችን የመለየትና አጀንዳ የማሰባሰብ ስኬታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም የህብረተሰቡን ፍላጎት በማካተት በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን የማደራጀትና ግብዓቶችን የማሰባሰብ ሥራ በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ግልጸኝነት፣ አካታችና ገለልተኝነት ለማስጠበቅም ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምሁራን፣ ሲቪል ማኅበራትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠቱን አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ግልጸኝነትና አካታችነት ምኅዳር ለማስጠበቅም በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጋር አጀንዳ ማሰባሰብና ተወካዮችን ማስመረጥ ያስቻለ ስኬታማ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል። በውጭ የሚኖሩ ዜጎች አጀንዳቸውን በማስረከብ ተወካዮቻቸውን የማስመረጥ ሥራም ተሰርቷል ብለዋል። በትግራይ ክልልም ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ምሁራን ጋር በሀገራዊ ምክክር ጉዳዮች ላይ በተለያዩ ጊዜያት ጥልቅ ውይይቶች መካሄዳቸውን አንስተዋል። በቀጣይም ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ምሁራን፣ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በማወያየት አጀንዳ የማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ ሥራ እንደሚከናወን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በዋና ዋና ሀገራዊ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ምክክር በማካሄድ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በማለም እየሰራ ይገኛል።
የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብርን ያጎለበተ ነው
Dec 20, 2025 60
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ክብር ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ያጎለበተ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኑነት ፖሊሲ ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን እያሳለጠ መሆኑንም ገልጸዋል። ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር፣ እኩልነትና የጋራ ተጠቃሚነት፣ በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባትና ለዓለም አቀፍ ስምምነቶች መገዛት የሚሉት አንድ ሀገር በውጭ ግንኙነት የሚከተላቸው ዋና ዋና መርሆች ናቸው። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትም ከትናንት እስከዛሬ ከራስ ብሔራዊ ጥቅም የሚቀዳ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተመሰረተ የኢኮኖሚና ቅድሚያ ለጎረቤት ዲፕሎማሲያዊ ትብብርን እያጎለበተ ይገኛል። ይህም የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ ገናና የሥልጣኔ ታሪክ ከአሁናዊ ዓለም ጋር በማሰናሰል ከብሔራዊ ክብርና ፍላጎት የተወዳጀ ፍሬያማ የዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትን በማጎልበት ወርቃማ ዕድል ሆኖ እያገለገለ ነው። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የዜጎችን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተደማጭነትና ልዕልና ለማስከበር አዎንታዊ ተፅዕኖ አላቸው ብለዋል። የመደመር እሳቤም የዜጎችን አንድነት በማስጠበቅ የኢትያጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ክብር ያስጠበቀና የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ያጎለበተ መሆኑን ገልጸዋል። የመደመር መንግስት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲና ቅድሚያ ለጎረቤት የሚሉት ወሳኝ መርሆች መሆናቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲም የውጭ ኢንቨስትመንትና የንግድ ትብብርን በማሳደግ የጋራ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ የትብብር መርህ መሰረት መሆኑን የአውሮፓ ሕብረትን በአብነት ጠቅሰዋል።   በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የስልጠና ክፍል ዳይሬክተር ጀነራል መላኩ ሙሉዓለም፤ ኢትዮጵያ በትብብርና አብሮ ማደግ ላይ የተመሰረተና በረጅም ታሪክ የዳበረ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ያላት ሀገር ናት ብለዋል። ኢትዮጵያ የብሪክስ (BRICS+) አባልነትን መቀላቀሏም የአፍሪካን ድምጽ በዓለም አቀፍ መድረኮች ለማንጸባረቅ የሚረዳ ወሳኝ የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በሰጥቶ መቀበል መርህ የዳበረውን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ዲፕሎማሲያዊ ትብብር በተሻለ የዕድገት ምዕራፍ ለማሳደግ እንደሚሰራ አስረድተዋል።
ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራዊ ምክክሩን እድል ልንጠቀምበት ይገባል-የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Dec 20, 2025 70
ሀዋሳ፤ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ) ፡-የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራዊ ምክክሩን እድል ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉ በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አካታችና አሳታፊ የሆነ ምክክር በማድረግ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር ይቻል ዘንድ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። በእስካሁኑ ሂደትም የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን በማገባደድ ወደ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ለመሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የምክክር ሂደቱንና አጠቃላይ የሚኖረውን ፋይዳ በተመለከተ ኢዜአ በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራርና አባላትን አነጋግሯል። የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊና የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ በለጠ ሲጌቦ፤ በዓለም ላይ የተለያዩ ሀገራት በምክክር ከመበተን ወደ አንድነት በመምጣት ዘላቂ ሠላም ማረጋገጥ መቻላቸውን አንስተዋል። በመሆኑም በኢትዮጵያ በሂደት ላይ ያለው ምክክር ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ከግጭት ለመውጣት ከምክክር የተሻለ እድልና አማራጭ የለም ሲሉም ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር በመሆኑ በአጀንዳ ላይ ተመካክሮ በመግባባት ችግሮችን በዘላቂነት መፍታትና ብሔራዊ መግባባት መፍጠር የሁላችንም ግዴታ ነው ሲሉ አንስተዋል። እንደ ፖለቲካ ፓርቲ አጀንዳችንን ለኮሚሽኑ ማቅረብ ችለናል ያሉት አቶ በለጠ፥ በምክክሩ በንቃት በመሳተፍ ለስኬታማነቱ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ዋና ሊቀመንበርና የጋራ ምክር ቤቱ አባል አቶ ለገሰ ላንቃሞ፤ የምክክር ሂደት የግጭትና ጦርነት ምክንያቶችን በመግባባት መቋጨት የሚያስችል ቁልፍ መፍትሄ በመሆኑ በትኩረት እየተሳተፍን እንገኛለን ብለዋል። ከመነሻው ጀምሮ በተሳታፊ ልየታም ሆነ በአጀንዳ ማሰባሰብ መድረኮች ላይ የፓርቲያቸው ተሳትፎ መኖሩን አንስተው፥ ለምክክሩ ሂደት ውጤታማነት እስከመጨረሻው እንሰራለን ሲሉም ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባሕል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ እና የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ኤርሚያስ፥ የፖለቲካ ስብራቶችን በማከም በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ፅኑ መሠረት እንዲኖረው መንግስት አበክሮ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፥ እየተንከባለሉ የመጡ ችግሮችን በመፍታት ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መመካከር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ከምክክር ውጭ የሚደረግ የሃይልና የጥፋት እንቅስቃሴ አንዳችም መፍትሄ የማያመጣ በመሆኑ ይህንን እድል ልንጠቀምበት ይገባል ብለዋል። የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት መመካከር ወሳኝ መሆኑን አንስተው፥ በአጀንዳዎቻችን ላይ በመምከር ለሀገርና ለትውልድ የሚበጅ ታሪክ እንስራ ሲሉ ተናግረዋል።
የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር በመሆን የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል-የቀድሞ ታጣቂዎች
Dec 20, 2025 79
ባሕርዳር፤ታሕሳስ 11/2018(ኢዜአ)፡-የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር በመሆን የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተን መጥተናል ሲሉ በአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ትጥቅ ይዘው ይንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ በመቀበል የተሀድሶ ስልጠና እየወሰዱ ወደ ማሕበረሰቡ መቀላቀላቸውን እንደቀጠሉ ነው። በዚህም መሰረት በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ፋግታ ላኮማ ወረዳ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በፈፀምነው ስሕተትና ባጠፋነው ጊዜ በመጸጸት ወደ ሰላማዊ ሕይወት ተመልሰናል ብለዋል። በሕዝብ ስም እየተማለ አምቡላንስን ማቃጠል፣ መሰረተ ልማቶችን ማውደም፣ ትምሕርት ቤቶች እንዲዘጉ ማድረግና ዘረፋ መፈፀም በቀጥታ ሕዝብን መጉዳት በመሆኑ ከጥፋታችን በመውጣት የሰላምን አማራጭ ተቀብለን መጥተናል ሲሉ ተናግረዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል ዘመነ አዲስ እና ገደፋው ሞላ፤ በአብዛኛው በጫካ ሲንቀሳቀስ የነበረው ታጣቂ በተሳሳተ እሳቤ በጥፋት መንገድ ላይ መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል እየገባ መሆኑን ገልጸዋል። በሕዝብ ስም እንታገላለን የሚል ማደናገሪያ ስለነበር ይህንኑ ሃሳብ በመቀበል ጫካ መግባታቸውን አንስተው በተግባር ሲታይ በሕዝብ ላይ ዘረፋ፣ እገታና ግዲያ መፈፀም በመሆኑ ይሕንን ተግባር በመቃወምና ሰላምን በመሻት መጥተናል ብለዋል። በመሆኑም የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር በመሆን የበደልውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተን መጥተናል ሲሉ ተናግረዋል። ሌሎች በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎችም መንግስት ያቀረበውን የሰላም እድል በመጠቀም መጥተው ሰላማዊ ሕይወታቸውን እንዲጀምሩ መክረዋል።   የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሃላፊ ጌታቸው ቢሻው፤ በዞኑ የሰላምን አማራጭ ተቀብለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማሕበረሰቡ እንዲቀላቀሉ እየተደረገ ነው ብለዋል። አሁንም ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት እያስረከቡ መግባታቸውን ቀጥለው እንዳሉ ጠቁመው፥ ይህም የሽፍታው ስብስብ እኩይ ተግባር በመገንዘቡ አብዛኛው የሰላም አማራጭን እየመረጠ ነው ብለዋል። መንግስት በሆደ ሰፊነት አሁንም የሰላም በሩን ክፍት በማድረግ መቀበሉን እንደሚቀጥል አረጋግጠው፥በሰላም የሚገቡትን የተሀድሶ ስልጠና በመስጠት ፍላጎታቸውን መሰረት በማድረግ የስራ እድል የመፍጠር ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። የሰላምን አማራጭ በማይቀበለው የሽፍታው ስብስብ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
በዞኑ የሕግ የበላይነትንና ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሕብረተሰቡን ያሳተፉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Dec 20, 2025 95
ቡሌ ሆራ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ) ፡- በምዕራብ ጉጂ ዞን የህግ የበላይነትንና ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሕብረተሰቡን ያሳተፉ የተቀናጁ ተግባራት ተጠናከረው መቀጠላቸውን የዞኑ አስተዳደርና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡ የጽሕፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ አየለ ደንባ፣ የመንግስትን የሰላም አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች መመለሳቸውን ቀጥለዋል ብለዋል። ወደ ሰላም የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችም የተሃድሶ ስልጠና እየወሰዱ ወደ ሕብረተሰቡ ተቀላቅለው መደበኛ ህይወት እንዲመሩ እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል። በቀጣይም በዞኑ የሕግ የበላይነትንና ሰላምን በዘላቂነት ለማስከበርና ለማፅናት ሕብረተሰቡን ያሳተፉ የተቀናጁ ተግባራት ተጠናከረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል።   የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ምክትል ኢንፔክተር ፈዬራ ኬይረዲን፤ የቀድሞ ታጣቂዎች በየቀኑ ወደ ሰላም መንገድ እየመጡ መሆኑን አንስተዋል። በተሳሳተ መንገድ ችግር ውስጥ ገብተው የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ሰላም እንዲመጡ አባገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሕዝቡ ተከታታይ ጥረት ሲያደርጉ እንደቆዩ አውስተው ፤ ይህም ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን አስረድተዋል። ከዞኑ ነዋሪዎች መካከል አባገዳ ጃርሶ ዱጎ፣ ከዞኑ ሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ከፍሎች ጋር በመሆን ለቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪ ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡ በዚህም በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች ባህልና እሴታቸውን እንዲሁም ቃላቸውን በማክበር እየተመለሱ በመሆኑ በዞኑ ሰላም ሰፍኗል ብለዋል፡፡ ችግርን በውይይት ከመፍታት በስተቀር እርስ በእርስ በመጎዳዳት የሚገኝ ጥቅም፤ የሚመጣ ለውጥም የለም ሲሉ ገልጸዋል፡፡ ወደ ሰላም ከተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል ሊበን ሸጋ በሰጠው አስተያየት፤ የሰላም አማራጭን ተቀብሎ በመመለስ የበደለውን ሕዝብ ለማካስ መዘጋጀቱን ገልጿል። በጫካ የቀሩትም የሰላም መንገድ በመምረጥ ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱም መልዕክት አስተላልፏል።
የሀገራዊ ምክክር ዕድልን መግፋት በምንም መልኩ አዋጭ አይደለም
Dec 19, 2025 154
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 10/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር የተመቻቸውን የጠረጴዛ ዙሪያ ሀገራዊ ምክክር ዕድልን መግፋት በምንም መልኩ አዋጭ አይደለም ሲሉ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ(ኢዜማ) ሥራ አስፈፃሚ አባል ግርማ ሰይፉ ገለጹ። ኢትዮጵያ የገጠሟትን ተግዳሮቶች ተቋቁማ ተዓምራዊ የዕድገት ለውጦችን እያስመዘገበች መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ(ኢዜማ) ሥራ አስፈፃሚ አባል ግርማ ሰይፉ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ቆይታ አድርገዋል። አቶ ግርማ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ እንዲመጣ ምክንያት የሆነው ለዘመናት የቆየው የዜጎች የጭቆና ትግልና የህልውና ጥያቄ ነው። በተለይም ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ የቀድሞው ገዥ ፓርቲ ኢሕአዴግ የራሱንና የአባላቱን ጥቅም ለማስጠበቅ በዜጎች ላይ የፈጠረው ኢ-ፍትሐዊ አስተዳደር፣ ሕዝቡ በአደባባይ እንዲታገልና ለውጥ እንዲመጣ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ግርማ፤ በአሁኑ ወቅት የተፈጠረውን የሀገራዊ ምክክር አውድ በመተው መሳሪያን በማንገብ የሚንቀሳቀሱ አካላት የዕውቀት አልባነት መገለጫ መሆኑን በጽኑ ተችተዋል። ነፃነት ካመጣው የሰለጠነ የምክክር አውድ ባፈነገጠ መልኩ፣ በነፃነት ስም በመሳሪያና በጉልበት መጓዝን የመረጡ ኃይሎች መፈጠራቸው ለሀገር ልማት እንቅፋት መሆኑን ነው የገለጹት። ባለፉት ሰባት ዓመታት ኢትዮጵያ በርካታ የግጭት ሴራዎችን ተቋቁማ ያስመዘገበችው ውጤት አስደናቂ መሆኑንና ተዓምራዊ የዕድገት ለውጦችን እያስመዘገበች ትገኛለች ሲሉ አብራርተዋል። ኢዜማ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጠረጴዛ ዙሪያ በመምከር መፍትሔ ማምጣትን እንደ ቀዳሚ አማራጭ እንደሚቀበል ገልጸውም፤ የትጥቅ ትግልን በመተው በሐሳብ የበላይነት መወያየት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኢዜማ ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የፖሊሲ አማራጭ ይዞ በመቅረብ፣ የአመራር አባላቱና ደጋፊዎቹ ለነቃ ፉክክር ዝግጅት እያደረጉ መሆኑም አስታውቀዋል። በምርጫ ቦርድ ዕውቅናው የተነሳው የቀድሞ ሕወሓት በክልሉ የሚያሳየው እብሪት መሠረተ ቢስና እውቀት አልባነትን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመው፤ የትግራይ ሕዝብ የፌዴራል መንግሥት ውክልናውን የሚያረጋግጥበትን አማራጭ እንዲፈጠርለት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪል ማኅበራት ሊሠሩ እንደሚገባ ተናግረዋል። በአንድ አንድ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ኃይሎችን በተመለከተ ምርጫውን የማደናቀፍ አቅም እንደሌላቸው ነው የገለጹት። የፓርቲያቸው የፖሊሲ አማራጮች ሌላውን የመጫን ፍላጎት እንደሌለው ጠቁመው፤ በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ሕዝብን በማስቀደም ለሀገር የሚጠቅም ውሳኔ ላይ መድረስ የጋራ ኃላፊነት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ማህበራዊ
ፍልሰት በአግባቡ ካልተመራ በዜጎችና ሀገር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያስከትላል
Dec 20, 2025 18
ወላይታ ሶዶ፤ታሕሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ፍልሰት በአግባቡ ካልተመራ በዜጎችና ሀገር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያስከትል ተገልጿል። በመሆኑም ፍልሰትን ወጥ በሆነ መንገድ በአግባቡ ለማስተዳደር የሁሉም ባለደርሻ አካላት ርብርብ ያስፈልጋል ተብሏል። "የዜጎች ፍልሰትን ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ኮንፈረንስ ዛሬ በሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። በኮንፍረንሱ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፈሰር ክንደያ ገብረህይወት በመድረኩ እንዳሉት፤ ፍልሰት በአግባቡ ካልተመራ በዜጎችና ሀገር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያስከትላል። ሆኖም በአግባቡ ማስተዳደር ከተቻለ የዜጎችንና የሀገርን ኢኮኖሚ ለመገንባት ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። ፍልሰትን በአግባቡ ለማስተዳደር የሁሉም ባለደርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥናትና ምርምር በማድረግ ፍልሰትን ወጥ በሆነ መንገድ ማስተዳደር ለሚያስችል ፖሊሲ ግብአት ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው አንስተዋል። ፍልሰትን በአግባቡ ማስተዳደር የሚያስችል በምርምር የታገዘ ስርዓት እንዲበጅ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚናን ለማጎልበት ሚኒስቴሩ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ፍልሰትን በምርምርና ጥናት በማገዝ ለዘላቂ ልማት ለማዋል ከአርባምንጭ፣ ዲላ እና ጂንካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር አብረው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በሀገሪቱ የግብርና፣ የማዕድን፣ ኢንዱስትሪና የቱሪዝም ልማት አካታችና ትርጉም ባለው መንገድ ለዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ካሠች ኤልያስ፤ ፍልሰትን ለዘላቂ ልማት ለማዋል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተጀመረው ጥረት የዘርፉን ችግር ለማቃለል አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። ህገ-ወጥ ፍልሰትን ለማስቆም ቢሮው ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በኮንፈረንሱ ላይ በፍልሰት ዙሪያ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
መንግስት የአብሮነት እሴቶችን በማጠናከር እያከናወናቸው የሚገኙ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል -ተሳታፊዎች
Dec 20, 2025 51
ቡታጅራ ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፡- መንግስት የአብሮነት እሴቶችን በማጠናከር በገጠርም ሆነ በከተማ እያከናወናቸው የሚገኙ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የቡታጅራ ከተማ የህዝባዊ ውይይት መድረክ ተሳታፊዎች ገለፁ፡፡ በከተማው "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሄዷል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች እንደገለፁት፤ መንግስት የአብሮነት እሴቶች እንዲጎለብቱ በማድረግ እያከናወናቸው የሚገኙ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል።   የውይይቱ ተሳታፊ ከሆኑት መካከል አቶ ወንደወሰን ኃይሌ አብሮነትን በማጠናከር የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመንግሥት በተጀመሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል። በዚህም በምስራቅ ጉራጌ ዞንና በማረቆ ልዩ ወረዳ መካከል ለረጅም ዘመናት ተከስቶ የነበረውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ መፍታት በመቻሉ በተጨባጭ የሚታይ ውጤት የተመዘገበበት ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ በቡታጅራ ከተማም ይሁን በአካባቢው የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማስቀጠልና ሰላማችንን በማስጠበቅ ከመንግሥት ጎን በመሆን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡   ሌላኛዋ የውይይቱ ተሳታፊ ወይዘሮ ከድጃ ሻፊ በበኩላቸው መንግሥት በአካባቢው ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በምግብ ራስን በመቻል ከተረጂነት ለመውጣት ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ጀምሮ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። በቡታጅራ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ስራን ጨምሮ ሌሎች የልማት ስራዎች የመጪውን ትውልድ ከግንዛቤ ያስገባ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ስራ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ክፍሉ ታምራት ናቸው፡፡ መንግሥት የኑሮ ውድነቱን ለመቆጣጠር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አምራቹንና ሸማቹን ህብረተሰብ በቀጥታ በማገናኘት እያከናወነ ያለውንን ተግባር ሊያጠናክር እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ እንዳሉት ክልሉ ያለውን የመልማት አቅም በመጠቀም ሁለንተናዊ ለውጥ ለማስመዝገብ ቅንጅታዊ ጉዞን ማጠናከር ይገባል፡፡   ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ እራስን ለመቻል የሚደረገውን ሀገራዊ ጥረት ለማገዝ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትግበራ ላይ የክልሉ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በተለያዩ መንገድ የሚከሰትን የኑሮ ውድነትን ለመከላከል ማህበረሰቡ በአካባቢው ያለውን ፀጋ አልምቶ በመጠቀም ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ለህግ አሳልፎ በመስጠት የሚጠበቅበትን ግዴታ መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በበኩላቸው የዞኑ አስተዳደር በቀጠናው ዘላቂ ሰላምን ከማስጠበቅ አንስቶ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   በዚህም በምስራቅ መስቃንና በማረቆ ልዩ ወረዳ የነበረውን የሰላም ችግርን በቅንጅት በመፍታት ማህበረሰቡን በልማት እንዲተሳሰር ስለመደረጉና የጋራ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ስራ ስለመጀመሩም ተናግረዋል፡፡ በከተማው የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ ማገናኘት የሚያስችሉ ከሰንበት እስከ የሰንበት የገበያ ማዕከላትን በማደራጀት ወደ ትግበራ መገባቱን የተናገሩት የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ ናቸው፡፡ በዚህም ምርት በተመጣጣኝ እንዲቀርብ እየተደረገ ስለመሆኑ ጠቅሰው በተለያየ መንገድ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ማህበረሰቡን ለምሬት የሚዳርጉ አካላትን የመቆጣጠር ስራ እንደሚጠናከርም ገልፀዋል፡፡  
የኢትዮ-ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትብብር የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያፋጥን የደቡብ ደቡብ ትብብር ወሳኝ መገለጫ ነው
Dec 20, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያና ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትብብር የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያፋጥን የ"ደቡብ-ደቡብ ትብብር" ወሳኝ መገለጫ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። የኢትዮጵያና ሕንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምርና ትምህርትን ትብብር ለማሳደግ ያለመ መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።   መርሃ-ግብሩም በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎችና በሕንድ ስመ-ጥር የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ትብብር በአምስት ዓመታት ውስጥ 1ሺ 200 የድህረ-ምረቃ(ፒኤችዲ) ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎችን ለማሰልጠን ዓላማ አድርጓል። በመርሃ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ፤ ኢትዮጵያና ሕንድ መካከል ረጅም ዘመናትን የተሻገረ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው ብለዋል። የኢትዮ-ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የትብብር መርሃ ግብርም በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ የሰው ሃብት በመፍጠር የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል። በትብብር መርሃ ግብሩ የተካተቱ ስምንት የሕንድ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶችም ችግር ፈቺ የምርምርና ፈጠራ ሥራዎችን በማካሄድ የደቡብ ደቡብ ትብብርን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በቅርቡ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝትም የሀገራቱን ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማሸጋገር እንዳስቻለ አስረድተዋል።   የኢትዮ-ሕንድ የጋራ የድህረ-ምረቃ ትምህርት አስተባባሪ ፕሮፌሰር ክሪሽና ራጅ፤ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውህሎትና በቴክኖሎጂ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ነው ብለዋል። በኢትጵያና ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል የተፈጠረው የትብብር አጋርነትም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ወሳኝ ሚና እንደሚጫዎት ገልጸዋል። ኢትዮ-ሕንድ የትምህርት የትብብር መርሃ-ግብር ማስጀመሪያ የተገኙት የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ታደሰ ረጋሳ (ዶ/ር)፤ መርሃ ግብሩ የሀገራቱን የትምህርት ትብብር ዘላቂ አጋርነትን ያረጋግጣል ብለዋል። የኢትዮ-ሕንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትብብር የሰው ሃብት ልማት አቅምን ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ያሉት ደግሞ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) ናቸው። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የሀገራቱ የምርምርና ትምህርት ተቋማት ትብብር የድህረ-ምረቃ ተማሪዎችን የምርምር ውጤት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያሳድጋል ብለዋል። መርሃ-ግብሩ ኢትዮጵያ ለጀመረችው የኢኮኖሚና የማህበራዊ ዕድገት የሚመጥን ብቁ የሰው ሃይል ለማፍራት በምታደርገው ጥረት ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረውም ተገልጿል።
ወጣቱ የሀገር ሽማግሌዎችን ምክርና የሰላም ግንባታ እሴቶችን ተቀብሎ በመተግበር ለሀገር ልማት መትጋት አለበት--የሀገር ሽማግሌዎች
Dec 19, 2025 107
ባሕርዳር፤ታሕሳስ 10/2018(ኢዜአ)፡- ወጣቱ ትውልድ የሀገር ሽማግሌዎችን ምክረ ሀሳብና የሰላም ግንባታ እሴቶች ተቀብሎ በመተግበር ለሀገር ልማት ይበልጥ መትጋት እንዳለበት የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተወጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች በዘላቂ ሰላም ግንባታ ዙሪያ በአማራ ክልል ባሕር ዳር ከተማ በጋራ ተወያይተዋል። ከውይይቱ በኋላ ኢዜአ ካነጋገራቸው የሀገር ሽማግሌዎች ከኦሮሚያ ክልል የመጡት አባ ገዳ ሀይሉ ለገሰ እንደገለጹት፤ የሽምግልና ስርዓትና የሰላም ግንባታ እሴቶች ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ የመጣ የችግሮች መፍቻ ቁልፍ መሳሪያ ነው። ወጣቱ ትውልድም ይህን የቆየ የኢትዮጵያዊያን የዳበረ ባሕላዊ እሴት በማክበርና በመቀበል ለሀገር አንድነት መፅናት ማዋል እንዳለበት መክረዋል። የሀገር ሽማግሌዎችም የአባቶችን ታሪክና አደራ ተቀብሎ የሚሰራና ግብረገብ የሆነ ወጣት በማፍራት በኩል ሃላፊነታችን በአግባቡ መወጣት አለብን ብለዋል። ከዘመናዊ ሕግ በፊት ጀምሮ ለዘመናት የዘለቀውን የሽምግልና ስርዓት በአግባቡ መጠቀም ላይ ክፍተት እየተስተዋለ መምጣቱን የገለጹት ደግሞ ከጋሞ የመጡት አቶ ብርሃኑ ደባልቄ ናቸው። ሽምግልና በሀገሪቱ የሕግ ጥላ ስር ሆኖ ችግሮች ሳይወሳሰቡ በአጭሩ መፍታት የሚያስችል የኢትዮጵያውያን እሴት ነው ብለዋል። በመሆኑም ወጣቱ በየአካባቢው ያሉ የቆዩ ችግር መፍቻ ባሕላዊ እሴቶችን እንደየ አካባቢው ሁኔታ የመረዳትና ለተግባራዊነቱ መትጋት እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል። የሀገር ሽማግሌ ለሰላም የሚተጋ፣ ለሀገር የሚቆረቆርና በዕድሜ ዘመኑ ያገኘውን ልምድ ተጠቅሞ ለእውነት የሚሰራ ነው ያሉት ደግሞ ከወላይታ የመጡት የሀገር ሽማግሌው አቶ ሰይፈ ለታ ናቸው። ሽምግልና የሰላም መግቢያ በር ነው ያሉት አቶ ሰይፈ፤ ይህንን የተቀደሰ እሴት ወጣቱ ትውልድ ተቀብሎ በመንከባከብና በመጠበቅ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንዳለበት መክረዋል። እርሳቸውም በአካባቢያቸው ለሚገኙ ወጣቶች በሃገር ሽማግሌዎች ሚና፣ በሽምግልና ስርዓት ምንነትና በሚያስገኘው ጠቀሜታ ላይ ግንዛቤ እየፈጠሩ መሆኑን አንስተዋል።  
ኢኮኖሚ
በምእራብ ወለጋ ዞን ሠላምን በማስፈን ለህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን እንደግፋለን --ነዋሪዎች
Dec 20, 2025 19
ጊምቢ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፡-በምእራብ ወለጋ ዞን ሠላምን በማስፈን ለህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን እንደግፋለን ሲሉ በጊምቢ ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ውይይት ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ገለጹ። ''የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ በዞኑ ከተለያዩ ወረዳዎች የተወጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ህዝባዊ ውይይት በጊምቢ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ የተሳተፉ የዞኑ ነዋሪዎች በዞኑ ሠላምን በማስፈን ረገድ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝቡን ጥያቄ የመለሱ ናቸው ብለዋል። ከለውጡ ዓመታት ወዲህ በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን አንስተዋል። በተለይም በህዝቡ ዘንድ የመልካም አስተዳዳር ችግር ሆነው የቆዩ መሰረተ ልማቶች ተቋማት ግንባታም በፍጥነት እየተከናወነ በመሆኑ መንግስትን አመስግነዋል። በቀጣይም ሠላምን በማስፈን ለህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን እንደግፋለን ሲሉ ተናግረዋል። ይሁን እንጂ አሁንም አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮች እልባት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ጠቁመው የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ እንዲፋጠን ጠይቀዋል። በተጨማሪም ህገ -ወጥ ንግድን ጨምሮ የኑሮ ውድነትን የሚያባብሱ ተግባራትን የመቆጣጠር ስራ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ሀላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ፣ የለወጡ መንግስት የህዝቡን ሁሉንተናዊ ህይወት ለማሻሻል እየተጋ ይገኛል ብለዋል። በተለይም በምዕራብ ኦሮሚያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ ህዝቡ ትኩረቱን ልማት ላይ እንዲያደርግ ማስቻሉን ገልጸው የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታም በስፋት መከናወኑን አንስተዋል። መንግስት የህዝቡን የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች የሚጠናከሩ ሲሆን የኑሮ ውድነትን ለመቀነስም ሰፋፊ እንቅስቃሴዎች ይደረጋሉ ብለዋል።   የምዕራብ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ በበኩላቸው በዞኑ ሰላምን በማፅናት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች ቀጥለዋል ብለዋል። በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎችን ማጠናከር እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቀነስ ዋና የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል።      
በኢሉአባቦር ዞን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ድሎች እንዲቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን --ነዋሪዎች
Dec 20, 2025 22
መቱ ፤ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ድሎች እንዲቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ በመቱ ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ውይይት ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ገለጹ። ''የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ከመቱ ከተማና ከኢሉአባቦር ዞን ወረዳዎች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮችን ያሳተፈ ህዝባዊ ውይይት በመቱ ከተማ ተካሄዷል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የዞኑን ህዝብ ተጠቃሚ ያደረጉ ታላላቅ የልማት ውጤቶች መመዝገብ ችለዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የመቱ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ሼህ ኤልያስ ሙሐመድ፣ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ልማቶች በሁሉም መስክ እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። ዘመናዊ የአሰራር ዘዴን በመከተል የግብርና ልማት በመተግበሩ ትልቅ ውጤት እየተመዘገበ የሕዝብን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላው ሊቀ ስዩማን ቀሲስ ታከለ ዳዲ በበኩላቸው መንግስት አንድነትን በማጽናት ልማትን ለማስፋፋት የሚያከናውነው ስራ የሚደገፍ ነው ብለዋል። በዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ድሎች እንዲቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ ተናግረዋል። አቶ ደበላ ዶርፎ በበኩላቸው በለውጡ ዓመታት መንግስት በሰላም፣ በልማት፣ በዲፕሎማሲ እና በሌሎች መስኮች ያሳየው ቁርጠኝነትና የተመዘገቡ ውጤቶች የሚያስመሰግኑ ናቸው ብለዋል። ሆኖም የዞኑንና የከተማውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችሉና ትኩረት የሚያሻቸው አንዳንድ ጉዳዮች አንዳሉም ተሳታፊዎቹ አንስተዋል። ከነዚህም መካከል የኖሌ- አልጌ- መቱ እንዲሁም የበቾ-ሳይለም-አጋሮ አስፋልት መንገዶች ግንባታ መጓተት፣ የአባቦር ስታዲየምና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ልማትን መፋጠን እንዳለባቸው ጠይቀዋል። የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት ሕዝቡ ከልማቱ ተጠቃሚ እንዳይሆን ትልቅ ተግዳሮት በመሆኑ መፍትሔ የሚሻ መሆኑንም አንስተዋል። በሌላ በኩል በዞኑ እየተተገበሩ የሚገኙ የሻይ እና የሩዝ ልማት ስራዎችን ተከትሎ የማቀነባበሪያ ፋብሪካ ሊታሰብበት ይገባል ሲሉም አንስተዋል። በዞኑ የሚገኘው ትልቅ የሀገር ሀብትና የቱሪዝም አቅም መሆን የሚችለው የሶር ፏፏቴ ስፍራ ልማት ትኩረት እንዲደረግበትም አክለዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ሻፊ ሁሴን፣ መንግስት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎችን በትኩረት እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ሕብረተሰቡም የስራ ባሕሉን ይበልጥ በማሻሻል ሁለንተናዊ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ እንዲተጋ ያሳሰቡት አቶ ሻፊ ዘላቂ ሰላም ለማስፈንም መትጋት ይገባል ነው ያሉት። የኢሉአባቦር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ፣ የሻይ ልማትን ጨምሮ ሌሎች አዳዲስ የግብርና ልማት ኢኒሼቲቮችን ለማስፋፋት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የህዳሴው ግድብ የኃይል አቅርቦት ለጤናው ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል ትልቅ አበርክቶ አለው
Dec 20, 2025 103
አሶሳ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል አቅርቦትን በማሳደግ ለጤናው ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል ትልቅ አበርክቶ እንዳለው የዘርፉ አመራሮች ተናገሩ። የጤና ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች፣ የሁሉም ክልሎች እና የሁለቱ ከተማ አስተዳደር የጤና ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች እና የሆስፒታል ስራ አስኪያጆች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል።   በጉብኝቱ ወቅት ያነጋገርናቸው የሥራ ኃላፊዎች እንደተናገሩት፤ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የዘመናት ቁጭት የመለሰ እና የይቻላል መንፈስን ያስመሰከረ ትልቅ ፕሮጀክት ነው። ከጎብኚዎቹ መካከል የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ብርሃኑ ሰንደቅ ግድቡን ለመጀመሪያ ጊዜ እየጎበኙ መሆኑን ገልፀው፥ ለግድቡ ባደረጉት ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ግድቡ በኃይል አቅርቦት ረገድ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ትልልቅ የጤና ተቋማት የሚያጋጥማቸውን የኃይል መቆራረጥ በማስቀረት ተገቢውን የህክምና አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል። በሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ የመድኃኒት እና ህክምና አስተዳደር ኃላፊ ነስረዲን አብዲ በበኩላቸው፤ ግድቡ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሚያስችሉ ፕሮጀከቶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። ህዳሴ ግድቡ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በጉባ ብስራቶች ላይ ይፋ ያደረጓቸው ፕሮጀክቶች በሶማሌ ክልል መጀመራቸውን ተናግረው፤ ፕሮጀክቶቹ ኢትዮጵያ በሁሉም አቅጣጫ የመልማት አቅም እንዳላት ማሳያ እንደሆኑም አብራርተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከመደገፍ ባሻገር ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል በመፍጠር በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓል ያሉት ደግሞ የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ጃፈር መርቀኒ እና በሲዳማ ክልል የዳዬ አጠቃላይ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ተሻለ ታምራት ናቸው። ግድቡ የጤና ተቋማት በቂ የኃይል አቅርቦት እንዲያገኙ እና የጤናው ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሻሻል የሚያደርግ ሀገራዊ ፕሮጀክት እንደሆነ አስታውቀዋል። አሁን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ በህዳሴው ግድብ ላይ ያሳየነውን አንድነት እና ትብብር አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል ብለዋል።      
የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ ለሌሎች ከተሞችም አርአያ የሆነና ተነሳሽነትን የፈጠረ ነው
Dec 20, 2025 82
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ለሌሎች ከተሞችም አርአያ የሆነና ተነሳሽነትን የፈጠረ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት አስተዳደር ባለስልጣን ገለጸ። የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ የከተሞች የኮሪደር ልማት ላይ ትኩረት ያደረገ ጉባኤ እያካሄደ ነው። በጉባኤው ላይ የከተሞች ከንቲባዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።   የአዲስ አበባ ከተማ የኮርደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት አስተዳደር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ከድር አደም በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በመጀመሪያውና በሁለተኛው ዙር ከ5 ሺህ 400 ሄክታር በላይ ለምቷል። በዚህም ከ179 ሺህ በላይ ሰዎች የሥራ እድል መፈጠሩን፣ የ185 ኪሜ የአስፋልት መንገድ ግንባታ እንዲሁም 47 ኪሜ የወንዞች ልማት መሰራቱን ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ስኬት ለሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞችም ምሳሌ የሚሆን ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ከተሞች ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑ ከማድረግ ባለፈ ለኢንቨስትመንት ሳቢ መሆን እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት የሰጠ ነው ብለዋል። በወንዝ ዳርቻ ልማቶችም የከተማዋን የተፈጥሮ ኃብቶች ወደ ውብ መዝናኛዎችና አረንጓዴ ሥፍራዎች መቀየሩን ጠቁመው፤ ሥነ-ምህዳር ከመጠበቅ አኳያም የተገኙ ውጤቶች ለነዋሪዎች ጤናና ሌሎች ጠቀሜታዎችን እንዲገኙ ማድረጉን አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ ዋና ዳይሬክተር አንዷአለም ጤናው በበኩላቸው፤የትብብር መድረኩ ከ137 በላይ ከተሞችን በአባልነት የያዘ መሆኑን ገልጸዋል። የትብብር መድረኩ ከተሜነትን በማስፋፋት የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ለማበርከት በመስራት ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ በከተሞች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ማነቆዎችን መፍታት የሚያስችሉ አማራጮችን በመቅረጽ፣ትስስርን ማጠናከርና የከተሞች የልምድ ልውውጥ ላይ እየሰራን ነው ብለዋል። የኮሪደር ልማት የከተማን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ማሻሻሉን አንስተዋል። በንግድ፣በመኖሪያ ቤት እና በኢንዱስትሪ ዞኖች መካከል ያለውን ትስስር፣ኢንቨስትመንቶችንና ንግዶችን በመሳብ የኢኮኖሚ እድገት ከማሳደግ አንጻር ያለውን ጠቀሜታዎችም ለአብነት አንስተዋል። ጉባኤው በኮሪደር ልማት በተምሳሌትነት የሚጠቀሱ የከተሞች ተሞክሮ የመማሪያ መድረክ መፍጠርን ያለመ መሆኑንም አስረድተዋል። የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ ሙራድ ከድር እና የከሚሴ ከተማ ከንቲባ ሸሪፍ ቃሲም በሰጡት አስተያየት ከአዲስ አበባና ከሌሎች ከተሞች በኮሪደር ልማት ስራዎች ከተመለከቱት ተሞክሮዎች መሰረት በማድረግ በከተሞቻቸው ህዝቡንና የግል ባለሀብቱን በማስተባበር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የሀገራችንን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረውን ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የትግበራ ምዕራፍ ዛሬ በይፋ አስጀምረናል-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Dec 20, 2025 0
ኢትዮጵያ የጀመረችውን ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ምርጫ ሳይሆን ግዴታችን ነው። ላለፉት አምስት ዓመታት ስንተገብረው የቆየነው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ሀገራችንን በቴክኖሎጂ የታገዘ የኢኮኖሚ መሠረት ላይ ለማቆም ያስቻሉ ተጨባጭ ውጤቶችን አስመዝግቧል። ከተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች መካከልም የዲጂታል መሠረተ ልማት፣ የሳይበር ምህዳር ደህንነት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ፣ ዲጂታል ፋይናንስና ክፍያ፣ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ዲጂታል ክህሎት የተላበሰ ብቁ ዜጋ መፍጠር ተጠቃሽ ናቸው።   አዲሱ ስትራቴጂ በተቀናጀ አመራርና በጠንካራ መዋቅር የሚመራ ሀገራዊ ስትራቴጂ ነው። ስትራተጂው ሁሉን አቀፍና አካታች የዲጂታል አገልግሎቶችን ተደራሽ ያደርጋል፤ ዜጎችን ማዕከል ያደረገ ዲጂታል መንግሥት ይገነባል፤ የሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችንና ስታርታፖችን ያበረታታል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት ከተለመደው አካሄድ ወጥተን፣ በፈጠራና በፍጥነት የታጀበ የዲጂታል ዝላይ ጉዞ ማድረግን ይጠይቃል። ለዚህ ደግሞ የመንግሥት ተቋማትና የግሉ ዘርፍ አገልግሎታቸውን ይበልጥ በማዘመን፣ የልማት አጋሮች ድጋፋቸውን ከስትራቴጂያችን ጋር በማጣጣም፣ ወጣቶችና ባለሙያዎች በፈጠራ አቅማቸው ሀገራዊ መፍትሔዎችን በማመንጨት፣ የድርሻቸውን እንዲወጡ አደራ እላለሁ። የኢትዮጵያን ብልፅግና በዲጂታል እውቀትና ፈጠራ እናሳካዋለን። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ አስጀመሩ 
Dec 20, 2025 25
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ):- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ዛሬ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ መጀመሩን ጠቁመው፤ ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል።   ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የተሟላ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ እያስቻለን ነው
Dec 20, 2025 59
ወልቂጤ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መያዛችን የተሟላ፤ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ እያስቻለን ነው ሲሉ የወልቂጤ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ። የዲጂታል ኢትዮጵያን እቅድ ለማሳካት እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ አገልግሎትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል። በዚህም መሰረት የፋይዳ መታወቂያን በመያዝ ዜጎች የሚፈልጉትን መንግስታዊና ማህበራዊ አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው የወልቂጤ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መያዛችን የተሟላ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ እያስቻለን ነው ብለዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል ወይዘሮ በላይነሽ ገብሬ፤ የፋይዳ መታወቂያ በተደራጀ መልኩ የተፋጠነ አገልግሎት እንድናገኝ እያስቻለን ነው ሲሉ ተናግረዋል። የመታወቂያውን አስፈላጊነት በመረዳትም ከራሳቸው ባለፈ ከ5 ኣመት በላይ የሆኑ ልጆቻቸው የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ እንዲያወጡ ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጭ አቶ መልስ ዶርጌ፤ የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ለአገልጋይም ሆነ ለተገልጋይ የተፋጠነ እና የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት ወሳኝ ስለመሆኑ ተናግረዋል። በአካባቢው የሚኖሩት ወጣት ጥላሁን ሸዋረጋ እና ወጣት ታገሱ ደጉ፤ የፋይዳ መታወቂያ በመያዛቸው በተለያዩ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት የተቀላጠፈ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ገልጸዋል። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ እና የፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ አገልግሎት ግብረ ሃይል አስተባባሪ ዳርጌ ተክሉ፤ በዞኑ እስካሁን በ58 ማእከላት 249 ሺህ 951 ዜጎች የፋይዳ ድጅታል መታወቂያ ተመዝግበው መውሰዳቸውን ተናግረዋል። በተያዘው በጀት አመትም 732 ሺህ 600 ዜጎች ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በአገልግሎት መስጫ ተቋማት ለዜጎች ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት እያስቻለ መሆኑን አንስተው፥ ሌሎችም መታወቂያውን በመያዝ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መክረዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት የዜጎችን የአገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል-ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ
Dec 20, 2025 79
ጅግጅጋ፤ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት የዜጎችን የአገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት የሚደረግ መሆኑን የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ገለጹ። በሶማሌ ክልል የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የተጀመረ ሲሆን በማስጀመሪያ መርሐግብር ላይ ሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ እንዲሁም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ እና ሌሎች የፌዴራል የክልሉ መንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ዛሬ አገልግሎት የጀመረው የጅግጅጋ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት በማስቀረት ፈጣን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል በመሆኑ ተጠያቂነትን ለማስፈንም እንደሚረዳ ተናግረዋል። ማዕከሉ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል ዘመናዊ መሰረተ ልማት እና የሰው ሀይል የተሟላለት መሆኑንም አንስዋል። አገልግሎቱን ለማስፋፋትም በቀጣይ በክልሉ 13 ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተግባራዊ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።   በመሆኑም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በሌሎች ከተሞችም በማስፋት የዜጎችን የአገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ በበኩላቸው፥ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ፣ ከአድሎ የጸዳ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።   የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ መንግሥትና ህዝብን የበለጠ የሚያቀራርብ እንዲሁም ሰው ተኮር የአገልግሎት ልህቀትን ለማረጋገጥም የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል። በአጠቃላይ ማዕከሉ መንግስት በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ የጀመረው ሪፎርም ለማሳካት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑንም አብራርተዋል። ዛሬ አገልግሎት የጀመረው ማዕከሉ 9 ተቋማትን በውስጡ የያዘ ሲሆን 32 አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተገልጿል።
ስፖርት
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት ከመገንባት ባለፈ ለብዝሃ ሕይወት መጠበቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው
Dec 20, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እያከናወነች ያለው ተግባር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት ከመገንባት ባለፈ ለብዝሃ ሕይወት መጠበቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ገለጸ። በኢትዮጵያ በየዓመቱ በስፋት የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነትና መሪነት የተጀመረ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ለመመከት፣ የአገሪቷን የደን ሽፋን ለማሳደግና በአረንጓዴ ልማት ላይ የተመሰረተ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያለመ ሲሆን፤ ባለፉት ዓመታት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሳተፍ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ በማድረግ ረገድ ዓለም አቀፍ እውቅናን ያተረፈ ስኬታማ ተግባር ተመዝግቧል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ካርታ ካስኬ (ዶ/ር) እንዳሉት ፤ የአየር ንብረት ለውጥ በብዝሃ ሕይወት ህልውና ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ በማሳደር ለሥነ-ምህዳር መመሰቃቀልና ለዝርያዎች መጥፋት ዋነኛ መንስኤ እየሆነ ይገኛል። ይህንን ስጋት ለመቀነስና የአየር ንብረት ለውጥን ለመመከት የሚከናወኑ ተግባራት ከፍተኛ ለውጥ እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እያከናወነች ያለው የችግኝ ተከላ ተግባር፣ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት እውን ለማድረግ መሠረት እየጣለ መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የገለጹት። እንደ ካርታ ካስኬ (ዶ/ር) ማብራሪያ፣ የምግብ ሥርዓት ከግብርና ምርታማነትና ከብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ፣ ኢንስቲትዩቱ ይህንን ሥርዓት ለማጠናከር የተለያዩ የአሰራር ስልቶችን ዘርግቶ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል። ለአብነትም የማህበራዊ ዘር ባንኮች ጥምረት አንዱ ሲሆን፤ ይህም በየአካባቢው ያሉና የማይበገር የምግብ ሥርዓትን እውን ማድረግ የሚያስችሉ የሰብል ዝርያዎችን መጠበቅ ያስችላል ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለአካባቢ ጥበቃና ደህንነት መረጋገጥ ትልቅ ማሳያ ተደርጎ እንደሚወሰድ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ይህም የብዝሃ ሕይወት ሀብትን በአግባቡ ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እያገዘው መሆኑን ገልጸዋል።
በጊምቢ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ንጹህ አካባቢን ፈጥሯል
Dec 19, 2025 114
ጊምቢ፤ ታህሳስ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በጊምቢ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተማዋን የቆሻሻ አወጋገድ ክፍተቶች በማረም ንጹህ አካባቢ እንዲኖረን አድርጓል ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነዋሪዎች፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ውብ እንድትሆን ከማድረግ ባለፈ የነዋሪዎችን የአኗኗር ዘይቤ እየቀየረ ስለመምጣቱም አክለዋል፡፡ የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት አቶ ኢዶሳ ገቢሳ፤ የኮሪደር ልማቱ በአካባቢያቸው ያለውን ሀብት እንዲገነዘቡ ከማድረግ ባለፈ ንጹህና ለኑሮ ምቹ አካባቢ መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡   በኮሪደር ልማት ስራው ልዩ የእግረኛ መንገድ፣ ንጹህ አረንጓዴ ስፍራና ውበትን የሚጨምሩ የመንገድ መብራቶች ዝርጋታ በመከናወኑ ለነዋሪዎች በእግር ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋ ውበትን እንድትጎናጸፍ እና በአኗኗር ዘይቤያችን ላይ ለውጥ እንዲመጣ አድርጓል ያሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ ላሊሳ ቡልቲ ናቸው።   በተጨማሪም የልማት ስራው ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ የቆሻሻ አወጋገድ ክፍተቶችን በመቅረፍ ንጽህናው የተጠበቀ፣ ተስማሚና ውብ አካባቢ እንዲኖረን አስቸሏል ብለዋል፡፡ ሸህ ሁሴን ጌታሁን የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው፤የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገጽታ በአጭር ጊዜ ውስጥ በመቀየር ውበትን እንድትጎናጸፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡   የጊምቢ ከተማ አስተዳዳር ከንቲባ አቶ ፈዬራ አቦማ፤በከተማዋ የኮሪደር ልማት ሥራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው ቀሪ ስራውን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የኮሪደር ልማቱ የእግረኛና የተሽከርካሪ መንገዶች እንዲሁም አረንጓዴ ስፍራዎችን አካቶ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው እስካሁን ወደ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚጠጋ የኮሪደር ልማት ስራ መከናወኑን አብራርተዋል።   በተለይም የኮሪደር ልማት ለዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩ በላይ ከዩኒቨርሲቲዎች ለተመረቁ ወጣቶች በትምህርት ቆይታቸው የቀሰሙትን በተገቢው በመተገበር ገቢ እንዲያገኙ እያስቻለ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ የጊምቢ ከተማን ለኑሮ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ከንቲባው አረጋግጠዋል፡፡
በዞኑ ከ251 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ይከናወናል
Dec 19, 2025 89
ጊምቢ፤ ታህሳስ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ወለጋ ዞን ከ251 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እንደሚከናወን ተገለጸ፡፡ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ከ33 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ማልማት መቻሉን ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል። ዘንድሮም ይኸው ተግባር በተለያዩ ክልሎች በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን በኦሮሚያ ክልልም የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው አርሶ አደሮችን ባሳተፈ መልኩ እየተካሄደ ነው። በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ከ3 ሚሊዮን ሄክታር በላይ የሚሆን መሬትን ወደ ልማት እንዲገባ በማድረግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የማጎልበት ስራ ተሰርቷል።   አሁን ላይም በክልሉ በሚገኙ ዞኖች የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን ከነዚሁ ዞኖች አንዱ በሆነው በምዕራብ ወለጋ ዞን በተያዘው የበጋ ወራት ከ251 ሺህ ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እንደሚከናወን የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት አስታውቋል። በጽህፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ እንደተናገሩት፤ በዞኑ በለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የአፈር መሽርሸርን በማስቀረት፣ የከርስ ምድርና ገጸ ምድር ውሀ ሀብት በመጨምርና የግብርና ምርታማነት በማሳደግ በኩል ተጨባጭ ለውጥ አምጥተዋል፡፡ በዘንድሮ በጋ ወራትም በ251 ሺህ 471 ሄክታር መሬት በላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸው በስራውም ከ400 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ አክለዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ በንቃት እንዲሳተፉ በማድረግ የእርከን ስራዎች፣ የውሃ መቀልበሻ ቦዮችና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል፡፡   ስራውን ለማሳካትም ካለፉት ዓመታት የተገኙ ልምዶችን በመቀመር የህብረተሰብ ንቅናቄ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል። ባለፉት ጊዜያት በተከናወኑት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ከልማት ወጪ የነበሩ አካባቢዎች ዳግም ወደ ልማት መግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአካባቢዎቹ መልማትም ህብረተሰቡ አካባቢውን እየጠበቀ ከልማቱ ጋር የተሳሰሩ እንደ የንብ ማነብ፣ የከብቶች መኖ ልማት እና ሌሎች የልማት ተግባራትን እንዲያከናውን ዕድል እንደተፈጠረለት ገልጸዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ፅዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት እያስቻሉ ነው 
Dec 18, 2025 102
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 9/2018 (ኢዜአ)፡-በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከናወኑ የአካባቢ ጥበቃና የልማት ስራዎች ፅዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት እያስቻሉ መሆኑ ተገለፀ። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የአካባቢ ጥበቃን በተመለከተ በወጡ ሕጎች፣ ደንቦች፣ ማዕቀፎችና አሰራሮች ላይ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለተውጣጡ ባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።   የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ በወቅቱ እንደገለጹት፤ መንግስት ባለፉት ጥቂት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ ያደረጋቸው የልማት ስራዎች ውጤታማ ናቸው። በተለይም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተከናወኑ ተግባራት ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ትልቅ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የአካባቢ ጥበቃና ልማት ስራዎችን በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል የሚያስችሉ የለውጥ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም አንስተዋል።   የአካባቢ ጥበቃ ስራ የመንግስት ወይም የአንድ ተቋም ኃላፊነት አለመሆኑን ያመለከቱት ዋና ዳይሬክተሯ፤ ህብረተሰቡንና የተለያዩ ተቋማትን በማስተባበር ቀጣይነት ያለው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ምርምር ማዕከል ኃላፊ ፕሮፌሰር በላይ ሰማኒ በበኩላቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎችን ከዘላቂ የልማት ግቦች በማቀናጀት ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ገልጸዋል።   ስለሆነም የአካባቢ ጥበቃ ፖሊሲዎችንና አዋጆችን በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል። የተመድ የልማት ፕሮግራም (UNDP) የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ባይድ ዶ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።   በተለይም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ እንዲሁም የካርበን ልቀትን ለመቀነስ የተከናወኑ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን በተጨባጭ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል። ይህ ስልጠናም በኢትዮጵያ የተጀመሩ የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎችን ከሀገራዊ የልማት ዕቅዶች ጋር አጣጥሞ ለማስኬድ የሚያስችል አቅም ይፈጥራል ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት ምን አሉ?
Dec 17, 2025 302
የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በአድዋ ድል መታሰቢያም የአበባ ጉንጉን አኑረዋል። ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት በስፋት ዘግበውታል። ዓለም አቀፍ የዜና ወኪሎቹ ሮይተርስ እና አሶሲዬትድ ፕሬስ ጉብኝቱን ከ"ጂኦ-ፖለቲካዊ" አንጻር ተመልክተውታል። በተለይ ህንድ በኢትዮጵያ ያላትን የአምስት ቢሊዮን ኢንቨስትመንት አጉልተዋል። አልጀዚራ ትኩረቱን ያደረገው ህንድ በ"ደቡባዊው ዓለም" (Global South) ላይ ያላትን ተጽዕኖ ለማሳደግ በምታደርገው ጥረት ላይ ነው። እንዲሁም የኢትዮጵያና የህንድ ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመካከለኛው ምስራቅና በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ፋይዳም በስፋት አንስቷል። ቢቢሲ እና ፍራንስ 24 ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለየት ያለ አቀባበል ትልቅ የዲፕሎማሲያዊ መቀራረብ ምልክት መሆኑን ዘግበውታል። የአፍሪካ ሚዲያዎች በበኩላቸው የናሬንድራ ሞዲን ጉብኝት "የአፍሪካ-ህንድ" ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ አድርገው ዘግበዋል። አፍሪካ ኒውስ እና ዘ ኢስት አፍሪካን ጉብኝቱ በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መደረጉን በማንሳት፣ ህንድ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ወታደራዊ፣ የጤና እና የቴክኖሎጂ ትብብር እንደሚያጠናክረውም ገልጸዋል። የደቡብ አፍሪካው ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ የናይጄሪያ እና ሌሎች የአፍሪካ መገናኛ ብዙሃን ህንድ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ኢትዮጵያን እንደ መግቢያ በር (Anchor) መጠቀሟን እና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የሚኖረውን ተምሳሌትነት ዘግበዋል። እንደ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ (The Times of India) ፣ ኤንዲቲቪ (NDTV) እና ኤኤንአይ (ANI) ያሉ የህንድ መገናኛ ብዙሃን የሞዲን ጉብኝት ከፍተኛ ሽፋን ሰጥተውታል። የዘገባዎቹ ዋንኛ ትኩረት በኢትዮጵያ ፓርላማ ስላደረጉት ንግግር እና ስለተደረገላቸው ልዩ የክብር ሽልማት ነው። በሌላ በኩልም የዲጂታልና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተደረጉ ስምምነቶችን በዝርዝር አቅርበዋል። አጠቃላይ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ትኩረት ታሪክ፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነት፣ የደቡብ ለደቡብ ትብብር ላይ ያጠነጠኑ ናቸው። የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ መሸጋገሩንም በመገናኛ ብዙሃኑ በስፋት ተነስቷል። ኢትዮጵያ እና ህንድ የተባበሩት መንግስታ ድርጅት እና ብሪክስን ጨምሮ በሌሎች የባለብዙወገን መድረኮች ላይ የደቡባዊውን ዓለም ድምፅ ለማሰማት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸው በዘገባዎቹ በስፋት ተንጸባርቋል።  
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 711
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል።   በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው።   አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 603
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
ሐተታዎች
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 435
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል።   ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ።   ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡   የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።  
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 780
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 975
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 998
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 563
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3044
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2982
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3883
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2440
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1565
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7384
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5869
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58530
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53032
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33703
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31234
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26925
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25718
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25275
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25224
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58530
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53032
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33703
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31234
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር  ተሻጋሪ ወዳጅነት 
Dec 16, 2025 316
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።  
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 870
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው።   እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም።   የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል።   የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል።   ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም