ኒውካስትል ዩናይትድ ቦዶ ግሊምት እና ባየር ሌቨርኩሰን ወደ ጥሎ ማለፍ ገብተዋል - ኢዜአ አማርኛ
ኒውካስትል ዩናይትድ ቦዶ ግሊምት እና ባየር ሌቨርኩሰን ወደ ጥሎ ማለፍ ገብተዋል
አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ ሶስት የመልስ ጨዋታዎች ተደርገዋል።
ኒውካስትል ዩናይትድ ካራባግን 3 ለ 2 አሸንፏል።
በሴንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሳንድሮ ቶናሊ፣ ጆሊንግተን እና ስቬን ቦትማን የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
ካሚሎ ዱራን እና ኤልቪን ጃፋርኩሊየቭ ለካራባግ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።
ኒውካስትል ዩናይትድ በድምር ውጤት 9 ለ 3 በማሸነፍ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅሏል።
በሌላኛው መርሐ ግብር ቦዶ ግሊምት ኢንተር ሚላንን 2 ለ 1 አሸንፏል።
በሳን ሲሮ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጀንስ ፒተር ሃውግ እና ሃልኮን ኢቭጄን የማሸነፊያ ግቦችን አስቆጥረዋል።
አሌሳንድሮ ባስቶኒ ለኢንተር ሚላን ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል።
ቦዶ ግሊምት በድምር ውጤት 5 ለ 2 በመርታት ጥሎ ማለፍ ገብቷል።
የሶስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ኢንተር ሚላን ጥሎ ማለፍ ሳይገባ ከውድድሩ ተሰናብቷል።
ባየር ሌቨርኩን ከኦሎምፒኮሶ ጋር ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
የጀርመኑ ክለብ በአጠቃላይ ውጤት 2 ለ 0 በማሸነፍ 16 ውስጥ ገብቷል።
ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ አትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ ብሩዥን በድምር ውጤት 7 ለ 4 አሸንፎ ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለዋል።