የእስራኤሉ ፕሬዝዳንት አይዛክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ - ኢዜአ አማርኛ
የእስራኤሉ ፕሬዝዳንት አይዛክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2018(ኢዜአ)፦ የእስራኤሉ ፕሬዝዳንት አይዛክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) እና ሚኒስትር ዴኤታው አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ፕሬዝዳንቱ በአዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ ከመንግሥት ከፍተኛ መሪዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።