ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የመውረድ ስጋት ያለበት ቶተንሃም ከሊድስ ዩናይትድ አቻ ተለያየ
May 12, 2026 68
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት ቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ሊድስ ዩናይትድ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማቲስ ቴል በ50ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠረው ጎል ቶተንሃም መሪ ሆኗል። ዶምኒክ ካልቨርት-ሉዊን በ74ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ያሳረፈው ጎል ሊድስ ዩናይትድን አቻ አድርጓል። በሊጉ ያስቆጠረውን ጎል ብዛት ወደ 13 ከፍ አድርጓል። በመጀመሪያው አጋማሽ ቶተንሃም፣ በሁለተኛው የጨዋታው ክፍለ ጊዜ ሊድስ ዩናይትድ የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል። ለረጅም ወራት በጉዳት ምክንያት ከሜዳ ርቆ የነበረው የቶተንሃም አማካይ ተጫዋች ጀምስ ማዲሰን ወደ ሜዳ ተመልሷል። ውጤቱን ተከትሎ ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ38 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። 18ኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው ዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ከፍ አድርጓል። የሰሜን ለንደኑ ክለብ አሁንም የመውረድ ስጋት አለበት። በሊጉ መቆየቱን ያረጋገጠው ሊድስ ዩናይትድ በ44 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ከቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ዌስትሃም ዩናይትድ ማን በሊጉ ይቆያል? ማን ይወርዳል? የሚለው ጉዳይ አጓጊ ሆኗል። ጨዋታውን ተከትሎ 36ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ከግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አሠራሩን ለማዘመንና ተወዳዳሪ ለመሆን እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ ነው
May 11, 2026 185
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አሰራሩን በማዘመን ከወቅቱ ጋር ለመዘመንና ተወዳዳሪ ለመሆን እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ። ቋሚ ኮሚቴው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የበጀት አፈፃፀምንና የ2019 በጀት ዓመት እቅድን ገምግሟል። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አመራሮች እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ላለፉት 85 ዓመታት የኢትዮጵያን ታሪክ በጽሑፍም በፎቶ ግራፍም ሰንዶ የያዘ አንጋፋ ተቋም ነው፡፡ በድርጅቱ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኤፍሬም ተክሌ፤ በአሁኑ ወቅት ዲጂታል ሚዲያው ለህትመት ሚዲያው ፈታኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። ድርጅቱም የዲጂታል ሚዲያውን መስፋፋት ታሳቢ አድርጎ እዩሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በህትመትም በዲጂታልም ተወዳዳሪና ተደራሽ ለመሆን ለዲጂታል አሰራሮች ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል፡፡ የድርጅቱ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወንድም ተክሉ በበኩላቸው፤ ድርጅቱ የራሱ የጋዜጣ እና መጽሔት ህትመት ቤት አለመኖሩ ለሥራው ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነበት ተናግረዋል፡፡ ይህ በተደጋጋሚ ሲነሳ የቆየ ችግር መሆኑን አንስተው፤ የጋዜጣና የመፅሔት ህትመት የየራሳቸው ባህሪ፣ ጥራትና ደረጃ የሚጠይቁ በመሆናቸው በተለያዩ ማተሚያ ቤቶች ለማሳተም እንደሚገደድ ጠቁመዋል። ለሁለቱም ህትመቶች የሚሆኑ ማተሚያ ቤቶች እንዲኖረው ቢደረግ የድርጅቱን አሠራር እንደሚያሻሽልና ወጪን እንደሚቀንስ ጠቅሰዋል። ከዚህም ባለፈ ለሌሎች ድርጅቶች ጭምር የህትመት አገልግሎት በመስጠት የገቢ ምንጭ ማድረግ እንደሚችልም አንስተዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ብዝኃነትን መሰረት ያደረገ የህትመት አቅምን ለማሳደግ እያደረገ ያለውን የሪፎም ሥራ አድንቀዋል። ድርጅቱ ከወቅቱ ጋር ለመዘመንና ተወዳዳሪ ለመሆን እያደረገ ያለው ተግባር የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ብለዋል። የድርጅቱ ማተሚያ ቤት ጥያቄ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ምክክር እንደሚደረግበትና እንደሚታይ ጠቁመዋል። ተቋሙ አሠራሩን ለማሻሻልና የገቢ አቅሙን ለማሳደግ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው
May 11, 2026 140
ሀዋሳ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን የበቆሎ ማሳ በመስክ ተመልክተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅት ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብዓቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። በክልሉ ያለውን የእርሻ አቅም አሟጦ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና በምግብ ራስን የመቻል ግብን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶች ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመው ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በበልግ ወቅት በክልሉ በሰብል የሚለማ የመሬት መጠን እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ አብዛኛው መሬት በምርጥ ዘር መሸፈኑን ተናግረዋል። የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ በበልግ እርሻ ከ152 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ዋና ዋና ሰብሎች እንዲሁም በስራስርና አትክልቶች መሸፈኑን ተናግረዋል። አጠቃላይ ከለማው መሬትም ከ24 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል። በልማቱ እየተሳተፉ ካሉ መካከል በሎካ አባያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ጽጌ ኩማ እንደገለጹት የአካባቢው 80 አርሶ አደሮች ከ75 ሄክታር በላይ ኩታ ገጠም መሬት ላይ በቆሎ እያለሙ መሆናቸውንና የማሳ እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሌላው በዳራራ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ዳዊት ብንኦ 40 ሆነው በኩታገጠም በቆሎ እያለሙ መሆናቸውን ጠቁመው ምርቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና በጋራ መስራታቸው ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት ተፈራረሙ
May 11, 2026 317
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ የምክክር ማዕቀፍ ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እና በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፖለቲካ ጉዳዮች አሊሰን ሁከር ፈርመዋል። በዚህ ስምምነት ኢትዮጵያና አሜሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ የሚያጠናክሩ የጋራ ትግበራ የሚሹ የትብብር አድማሶችን በማስፋት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። የተፈረመው የሁለትዮሽ መዋቅራዊ ምክክር በየዓመቱ አንዴ አዲስ አበባ ሌላ ጊዜ ዋሽንግተን ዲሲ የሚካሄድ ሲሆን የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ስብሰባውን በጋራ የሚመሩት ይሆናል። ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሹ መዋቅራዊ ምክክር ሦስት ምሰሶዎችን ያካተተ እንዲሆን ተስማምተዋል። አንደኛው የኢኮኖሚ ብልጽግናን፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት የሚዳስስ ሲሆን በዚህ ክፍል የሁለትዮሹን ኢኮኖሚያዊ እና የንግድ ትስስር የበለጠ ማጠናከርና ኢንቨስትመንት እና ንግድን ለማስፋት እንደሚሰራ ተገልጿል። ሁለተኛው የመከላከያ እና ጸጥታ ትብብርን የሚመለከት እንደሆነና የጸጥታ ጉዳይ ትብብርን ማጠናከርና በጋራ የደኀንነት ጉዳዮች ዙሪያ ተሳትፎን ማጠናከርን ያካትታል። የመጨረሻው እና ሦስተኛው ምሰሶ ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋትን የተመለከተ ሲሆን በዚህ ክፍል የጋራ ጥቅምን እንዲሁም ቀጣናዊ ሰላምንና ደኀንነትን የሚያስጠብቁ አካሄዶችን በመፈተሽና በትብብር መሥራትን ያረጋግጣል። ይህ ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ዘላቂ በሆነ መንገድ የሚያስቀጥልና የሚያጠናክር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ቦሌ ክፍለ ከተማ ድል ቀንቶታል
May 11, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቦሌ ክፍለ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ምህረት አየለ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። የግቦቹ ባለቤት ምህረት አየለ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። በሊጉ 12ኛ ድሉን ያስመዘገበው ቦሌ ክፍለ ከተማ በ43 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ከሁለት ተከታታይ ድሎች በኋላ የተሸነፈው ሸገር ከተማ በ47 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ረግቷል። በውድድር ዓመቱ በአጠቃላይ ስድስተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ የ26ኛ ሳምንት ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ እና መቻል ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት ተፈራረሙ
May 11, 2026 317
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ የምክክር ማዕቀፍ ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እና በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፖለቲካ ጉዳዮች አሊሰን ሁከር ፈርመዋል። በዚህ ስምምነት ኢትዮጵያና አሜሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ የሚያጠናክሩ የጋራ ትግበራ የሚሹ የትብብር አድማሶችን በማስፋት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። የተፈረመው የሁለትዮሽ መዋቅራዊ ምክክር በየዓመቱ አንዴ አዲስ አበባ ሌላ ጊዜ ዋሽንግተን ዲሲ የሚካሄድ ሲሆን የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ስብሰባውን በጋራ የሚመሩት ይሆናል። ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሹ መዋቅራዊ ምክክር ሦስት ምሰሶዎችን ያካተተ እንዲሆን ተስማምተዋል። አንደኛው የኢኮኖሚ ብልጽግናን፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት የሚዳስስ ሲሆን በዚህ ክፍል የሁለትዮሹን ኢኮኖሚያዊ እና የንግድ ትስስር የበለጠ ማጠናከርና ኢንቨስትመንት እና ንግድን ለማስፋት እንደሚሰራ ተገልጿል። ሁለተኛው የመከላከያ እና ጸጥታ ትብብርን የሚመለከት እንደሆነና የጸጥታ ጉዳይ ትብብርን ማጠናከርና በጋራ የደኀንነት ጉዳዮች ዙሪያ ተሳትፎን ማጠናከርን ያካትታል። የመጨረሻው እና ሦስተኛው ምሰሶ ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋትን የተመለከተ ሲሆን በዚህ ክፍል የጋራ ጥቅምን እንዲሁም ቀጣናዊ ሰላምንና ደኀንነትን የሚያስጠብቁ አካሄዶችን በመፈተሽና በትብብር መሥራትን ያረጋግጣል። ይህ ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ዘላቂ በሆነ መንገድ የሚያስቀጥልና የሚያጠናክር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በኢትዮጵያ እና ቻይና መካከል ያለው በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ሀገራቱን አስተማማኝ የልማት አጋሮች አድርጓቸዋል
May 11, 2026 222
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እና ቻይና መካከል ያለው በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ሀገራቱን አስተማማኝ የልማት አጋሮች እንዳደረጋቸው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቻይና ሕዝብ ብሔራዊ ኮንግረንስ የልዑክ ቡድን አባላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ ኢትዮጵያ እና ቻይና እ.አ.አ ከ2023 ጀምሮ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን በሁኔታዎች ወደማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነት አሳድገዋል፡፡ ሁለቱ ሀገራት በዓለም አቀፍ የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እርስ በርስ በመደጋገፍ ግማሽ ክፍለ ዘመን የተሻገረ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሥርተዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲን ትደግፋለች፡፡ የአፍሪካ ሀገራትን ተጠቃሚ በሚያደርገው የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር ዝርጋታን ጨምሮ በተለያዩ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች ተጠቃሚ መሆኗን ገልጸዋል፡፡ ቻይና የኢትዮጵያ አስተማማኝ አጋር መሆኗን ገልጸው፤ የኢትዮጵያ የግብርና፣ ማዕድን፣ የጨርቃጨርቅና ሌሎች ምርቶች ቀዳሚ ተቀባይ ሀገር ሆናለች ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የቻይና ኩባንያዎች የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት አምስት ቢሊየን ዶላር መድረሱን በመጥቀስ፤ ከሁለት ሺህ በሚልቁ ፕሮጀክቶች ከ560 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል፡፡ በደቡብ ደቡብ እና በቻይና-አፍሪካ ማዕቀፍ የሁለቱ ሀገራት ትብብር ጠንካራ መሰረት ያለው መሆኑን በመግለጽ፤ ኢትዮጵያ ለውጭ ኢንቨስትመንት ትርጉም ያለው የቢዝነስ ከባቢ ፈጥራለች ብለዋል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ትብብር እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ በበርካታ ዘርፎች የትብብር ስምምነቶችን በመፈራረም በተግባር የሚገለጽ ውጤት ማስመዝገባቸውን አንስተዋል፡፡ የሁለቱ ሀገራት የሕግ አውጪዎች የውይይትና የልምድ ልውውጥ መድረክ የሕዝብ ለሕዝብና የተቋማት ትብብርን ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን እምቅ የባህልና የቅርስ ሀብት ለቱሪዝም ልማት ማዋል እንዲችሉ በትብብር እንሰራለን ብለዋል፡፡ የቻይና ብሔራዊ ኮንግረንስ የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ባህልና የማህበረሰብ ጤና ኮሚቴ ሊቀ መንበርና የልዑኩ መሪ ሉ ሹጋንግ ወደ ኢትዮጵያና ውቧ አዲስ አበባ ለጉብኝት በመምጣታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና ቻይና በባህል፣ ቅርስና በቱሪዝም ሀብት የታደሉ ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የሁለቱ ሀገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እየተጠናከረ መጥቷል ነው ያሉት፡፡ በሁለቱ ሀገራት ምክር ቤቶች መካከል የሚደረገው እውነተኛ ትብብር በማንኛውም ጊዜ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ እና ቻይና የረጅም ጊዜ ትብብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ አመራር ሰጪነት በሁኔታዎች ወደማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማደጉን አውስተዋል። ሀገራቱ በዓለም አቀፍ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እርስ በርስ እንደሚደጋገፉ በማንሳት፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸው አድማሱን እያሰፋ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ ቻይና የተፈረሙ ስምምነቶች በፍጥነት እንዲተገበሩ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸው፤ የሀገራቱ ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክር ቤቶቹም በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ናቸው ብለዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት፣ ስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ ዘርፎች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ላለው በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂያዊ አጋርነት ትልቅ ዋጋ እንደሚሰጡ በማንሳት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ዓመታት በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ሪፎርም ማድረጓን ለቻይና ልዑክ አብራርተዋል፡፡ በሪፎርሙ የመንግስትን አገልግሎት በዲጂታል የታገዘ በማድረግ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን መልካም አስተዳደርን የማስፈን ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል፡፡ የፖለቲካ ሪፎርሙ ሰላማዊ ትብብርና ተሳትፎን የሚያረጋግጥ ምህዳር በመፍጠር የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አሳድጓል ብለዋል፡፡
በፓርቲው መሪነት ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
May 11, 2026 212
ባህርዳር፣ደሴ፣ገንዳ ውሃ ፤ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፡- በብልፅግና ፓርቲ መሪነት ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። የብልፅግና ፓርቲ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ የምርጫ ማኒፌስቶውንና የዕጩዎች ትውውቅ መድረኩን በባህርዳር፣ ደሴና ገንዳ ውሃ ከተሞች አካሂዷል። በብልጽግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በፓርቲው መሪነት በከተማዋ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የተለያዩ የልማት ስራዎች ተካሂደዋል ። የጣና ዳር አረንጓዴ ልማትና የኮሪደር ልማት፤ የአባይ ድልድይ እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ የአስፋልት መንገዶችና ሌሎች የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ከተማዋን ለቱሪዝም፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ማድረግ መቻሉን አመልክተዋል። ፓርቲው በቀጣይም መሰል የልማት ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። በተያያዘ ዜና በብልጽግና ፓርቲ የደሴ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁ በመድረኩ እንደገለፁት፣ የብልጽግና ፓርቲ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። የልማት ፕሮጀክቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የምርጫውን ሰላማዊነት ማረጋገጥ ላይ በማተኮር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የደሴ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፣ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ዳር ለማድረስ እንደሚሰራ ተናግረዋል። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የአስተዳደር ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጥላሁን መኳንንት በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ እንደገለጹት ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ክትትልና ድጋፍ እያደረገ ነው። ምርጫው የህዝብ ድምፅ የሚከበርበትና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ብልጽግና ፓርቲ በመደመር እሳቤ በሰው ተኮር የልማት ሥራዎች ውጤት አስመዝግቧል
May 11, 2026 328
ሳጃ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ብልጽግና ፓርቲ በመደመር መንግስት እሳቤ ጠንካራ ተቋማት በመገንባትና በሰው ተኮር የልማት ሥራዎች ውጤት ማስመዝገቡን በፓርቲው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገለጸ። ፓርቲው "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ አባላቱና ደጋፊዎቹ በተገኙበት ዛሬ በየም ዞን ሳጃ ከተማ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል። በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፓርቲው በለውጡ ዓመታት ባከናወናቸው ተግባራት ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ሰጥቷል። በመደመር መንግስት እሳቤ በመመራት ጠንካራ ተቋማትን ከመገንባት ባለፈ የተለያዩ ሰው ተኮር የልማት ሥራዎችን አከናውኗል ብለዋል። ብልጽግና ፓርቲ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ አበክሮ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሺመልስ እጅጉ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ዞኑ በለውጡ ዓመታት የአካባቢውን ጸጋዎች ከሰው ኃይል ልማት ጋር አቀናጅቶ ባከናወናቸው የልማት ሥራዎች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። በዚህም በመሰረተ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት እና በአትክልት ልማት ከመቼውም ጊዜ በላይ ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር ላቀዳቸው የልማት ግቦች መሳካት ህዝቡ ከፓርቲው ጎን በመሰለፍ በጠቅላላ ምርጫው ይሁንታውን እንዲሰጠውም ጥሪ አቅርበዋል። በምርጫ ቅስቀሳው ከተሳተፉት መካከል አቶ ንጉሴ ራያ እና የደሪ ዙርያ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ብርቱካን ሙራስ እንዳሉት፤ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች በተሰሩ ሥራዎች የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ መጥቷል። የብዙ ጊዜ ጥያቄያቸው የነበረው የዞን መዋቅር ምላሽ ማግኘቱን የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ በአካባቢው ስንዴ፣ አትክልትና ፍራፍሬ በስፋት በማምረት ኢኮኖሚያዊ እድገት እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል ። በተለይም በሳጃ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር፣ የመንገድ፣ የወጣቶች መዝናኛ እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ለማስቀጠል ከፓርቲው ጎን በመሆን እንደሚንቀሳቀሱም አረጋግጠዋል።
በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ ናቸው
May 11, 2026 221
ቦንጋ፤ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤቶች በብልፅግና ፓርቲ ከቀረቡ ዕጩዎች ጋር የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ በብልጽግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ ፍትሀዊ የልማት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በተሰራው የተቀናጀ ስራ ስኬት መመዝገቡን ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን አመልክተዋል። የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እንዲበቁ ከማድረግም ባለፈ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በመጀመር ሰፊ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም በመንገድ፣በድልድይና በሌሎችም መሰረተ ልማቶች ውጤት መመዝገቡን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ዘርፍ በትምህርትና በጤና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ተናግረዋል። መድረኩ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሀዊና ተዓማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ተልዕኮዎቹን ለማላቅና የጋራ ዓላማ ለመያዝም የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል። በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፥ ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ትልልቅ ሀገራዊ ተልዕኮዎችን ሲያስፈፅምና ሲፈፅም መቆየቱን ገልፀዋል። ለውጡን ለማስረፅና ለማፅናት እንዲሁም የብልፅግና ጉዞን ለማሳለጥ ርብርብ ሲደረግ ቆይቷል ያሉት አቶ ፍቅሬ፥ በሂደቱም በርካታ ሪፎርሞችን በመተግበር ውጤታማ መሆን ተችሏል ብለዋል። የክልሉ ሕዝቦች የዘመናት ጥያቄ ሆኖ የቆየው በክልል መደራጀት ምላሽ ካገኘበት ማግስት ጀምሮ በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በተመዘገቡ ውጤቶች የህዝቡ ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መምጣቱንም ተናግረዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ዲሞክራሲያዊና ፍትሃዊ እንዲሆን በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በመድረኩ ባለፉት አምስት ዓመታት በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች የተሰሩ ስራዎችና የተመዘገቡ ውጤቶች ላይ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።
ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላችንን እየተወጣን ነው- ተፎካካሪ ፓርቲዎች
May 11, 2026 212
ደሴ ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተፎካካሪ ፓርቲዎች ገለፁ። ጠቅላላ ምርጫው የህዝብ ተሳትፎ የተረጋገጠበትና ፍትሀዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ለአባላትና ለደጋፊዎቻቸው ግንዛቤ ከመፍጠር ባለፈ የምርጫ ህጉን ተከትለው እንዲሰሩ ማድረጋቸውን ፓርቲዎቹ ገልጸዋል። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ያላቸውን የፖሊሲ አማራጮች ከማስተዋወቅ ባለፈ ዴሞክራሲያዊ ሥርአቱ እየጎለበተ እንዲመጣ ለሀሳብ የበላይነት እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲ ፓርቲ የምርጫና ዴሞክራሲ ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ የሺበር ጌጡ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲውን አማራጭ ሀሳብ ለህዝብ እያስተዋወቁ ነው። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅትም ሆነ በምርጫው እለት አባሎቻቸውም ሆኑ ደጋፊዎቻቸው የምርጫ ህግን እንዲከተሉ በማድረግ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና አሳታፊነት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለፖለቲካ ፓርቲዎች የተፈጠረው ምቹ ምህዳር ህብረተሰቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የፖሊሲ አማራጭና ራዕይ ተረድቶ የሚፈልገውን ፓርቲ መምረጥ የሚችልበት አውድ ለመፍጠር ማስቻሉንም ገልጸዋል። "የሰላም ለኢትየጵያ ጥምር ፓርቲ" የምርጫና የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊና የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ፕሬዚዳንት አቶ አላምረው ይርዳው እንዳሉት፤ በጠቅላላ ምርጫው ፓርቲያቸው ሰላምና ልማትን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለህዝብ በተለያየ መንገድ አስተዋውቋል። በምርጫው ጠንካራ ፉክክርና ክርክር ከማድረግ ባለፈ ተዓማኒ፣ ሰላማዊና አሳታፊ እንዲሆን አበክረው እየሰሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ምርጫ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት አንዱና ወሳኝ በመሆኑ በሀሳብ የበላይነት ለማሸነፍ እየተወዳደሩ መሆናቸውን ያነሱት ደግሞ የአንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የቦርድ አባል አቶ ዮሴፍ አሻግሬ ናቸው። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን አባሎቻቸውና ደጋፊዎቻቸው የድርሻቸውን እንዲወጡ የማስገንዝብ ሥራ መስራታቸውን ገልጸዋል፡፡
ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችንን እንወጣለን- የምስራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች ክልሎች ሴቶች
May 10, 2026 433
ድሬደዋ ፣ ግንቦት 2/2018(ኢዜአ):- የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ የምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎች ሴቶች አስታወቁ። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን ለምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎች ሴቶች በድሬደዋ ያዘጋጀው የምርጫ ታዛቢነት የአሰልጣኞች ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል። በስልጠናው ላይ የተሳተፉት የድሬደዋ አስተዳደር፣ የሐረሪ እና የሶማሌ ክልሎች ሴቶች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ለሁለት ቀናት የተሰጣቸው ስልጠና በዘንድሮ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ የተጣለባቸው የታዛቢነት ኃላፊነት በላቀ ብቃት ለመወጣት ያስችላቸዋል። ከሶማሌ ክልል ጅግጅጋ የተሳተፉት ወይዘሮ ከድራ ኢብራሂም እንደተናገሩት፤ የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ታአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በትኩረት እየሰሩ ናቸው። በተለይም በምርጫው የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና የውሳኔ ሰጪነት ሚና እንዲጎለብት እየሰሩ መሆኑን በመግለፅ። ለሁለት ቀናት የተሰጠን የምርጫ ታዛቢነት የአሰልጣኞች ስልጠና በምርጫው ያለብንን ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት ያስችለናል ያሉት ደግሞ ከሐረሪ ክልል ሴቶች ፌደሬሽን የተሳተፉት ወይዘሮ ነጃሃ ኡመር ናቸው። የቀሰምነውን ዕውቀት በየክልሎቻችን ለሚገኙ የምርጫ ታዛቢ ሴቶች በማካፈል በጠቅላላው ምርጫ ህግና ደንብ በአግባቡ እንዲተገበር የድርሻችንን ኃላፊነት ለመወጣት ያስችለናል ብለዋል። ከድሬደዋ አስተዳደር የሴቶች ፌዴሬሽን የተሳተፉት ወይዘሮ ቅድስት አየለ በበኩላቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች በመራጭነት፣ በተመራጭነት እና በታዛቢነት በመሳተፍ ምርጫው በህዝብ ዘንድ ቅቡል እና ፍፁም ታአማኒ ሆኖ እንዲካሄድ የተቀናጀ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል። በአስተዳደሩ በምርጫ ታዛቢነት የሚሳተፉ ሴቶች የታዛቢነት መብትና ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲገነዘቡ መደረጉ ኃላፊነትን በትክክል ለመወጣት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል ። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ትዕግሥት ተረፈ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና የውሳኔ ሰጪነት ሚና እንዲጎለብት ውጤታማ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። ፌዴሬሽኑ በሀገሪቱ በሁሉም አቅጣጫዎች የሚገኙ ሴቶች በሁሉም መስክ ተሳትፏቸው እንዲጨምር መስራቱን ጠቅሰው በፌዴሬሽኑ በ54 የተለያዩ አደረጃጀቶች የታቀፉ ሴቶች አባላቱ በምርጫው የላቀ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን አንስተዋል። በዘንድሮ ምርጫ ላይ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ 10 ሺህ ሴቶች ነፃ እና ገለልተኛ ሆነው በታዛቢነት ይሳተፋሉ ብለዋል።
ፓርቲው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በማስቀጠል የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበልጥ ይሰራል
May 10, 2026 411
ገንዳውኃ/ደብረ ብርሃን ፤ግንቦት 2/2018(ኢዜአ)፡- የብልጽግና ፓርቲ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በማስቀጠል የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበልጥ እንደሚሰራ አስታወቀ። የብልጽግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ በምዕራብ ጎንደር ዞንና ደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ ዛሬ አካሂደዋል። የምእራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ ባስተላለፉት መልእክት እንደገለጹት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ለማስቀጠል ሰላማዊና ፍትሃዊ ምርጫን ማካሄድ ተገቢ ነው። ብልጽግና ፓርቲም ይህንኑ ለመተግበር ለአባላትና ለደጋፊዎቹ ጭምር የምርጫ ስነምግባር ማስተማሩን ተናግረዋል። በሰልፉ ላይ የተገኙት የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪ አቶ እንዳላማው ማሩ በበኩላቸው በከተማዋ የተከናወኑ የኮሪደር፣ የመንገድ፣ የወጣቶች መዝናኛና የስፖርት ማዘውተሪያ እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል። ይህን ለማስቀጠል የሚሆነን ፓርቲ መምረጥ ይገባናል ብለዋል። በተያያዘ ዜና በደብረ ብርሃን ከተማ በተካሄደው የምርጫ ቅስቀሳ መልእክት ያስተላለፉት የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት እንደ ሀገር የተፈጠረው አካታች የፖለቲካ ምህዳርን በመጠቀም የብልጽግና ፓርቲ የፖሊሲ አማራጮቹን ይዞ ቀርቧል። የተመዘገበውን ሀገራዊ እድገት ለማስቀጠል ፓርቲው ጠንክሮ እንደሚሰራም ጠቁመዋል። በከተማ አስተዳደሩ ባለፉት አምስት ዓመታት የተገኘውን እድል በማስፋት ከተማዋን የቱሪዝም፣ የኢንቨስትመንትና የንግድ ማእከል ለማድረግ የዘንድሮውን ምርጫ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር እየተሰራ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳው ከተሳተፉት መካከል አቶ ዘሪሁን ከበደና አቶ ዓለማየሁ ሸዋንግዛው እንዳሉት በብልጽግና ፓርቲ የተጀመሩ የሰላምና የልማት ትሩፋቶችን ለማስቀጠል በምርጫው በንቃት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት ተፈራረሙ
May 11, 2026 317
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ የምክክር ማዕቀፍ ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እና በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፖለቲካ ጉዳዮች አሊሰን ሁከር ፈርመዋል። በዚህ ስምምነት ኢትዮጵያና አሜሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ የሚያጠናክሩ የጋራ ትግበራ የሚሹ የትብብር አድማሶችን በማስፋት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። የተፈረመው የሁለትዮሽ መዋቅራዊ ምክክር በየዓመቱ አንዴ አዲስ አበባ ሌላ ጊዜ ዋሽንግተን ዲሲ የሚካሄድ ሲሆን የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ስብሰባውን በጋራ የሚመሩት ይሆናል። ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሹ መዋቅራዊ ምክክር ሦስት ምሰሶዎችን ያካተተ እንዲሆን ተስማምተዋል። አንደኛው የኢኮኖሚ ብልጽግናን፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት የሚዳስስ ሲሆን በዚህ ክፍል የሁለትዮሹን ኢኮኖሚያዊ እና የንግድ ትስስር የበለጠ ማጠናከርና ኢንቨስትመንት እና ንግድን ለማስፋት እንደሚሰራ ተገልጿል። ሁለተኛው የመከላከያ እና ጸጥታ ትብብርን የሚመለከት እንደሆነና የጸጥታ ጉዳይ ትብብርን ማጠናከርና በጋራ የደኀንነት ጉዳዮች ዙሪያ ተሳትፎን ማጠናከርን ያካትታል። የመጨረሻው እና ሦስተኛው ምሰሶ ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋትን የተመለከተ ሲሆን በዚህ ክፍል የጋራ ጥቅምን እንዲሁም ቀጣናዊ ሰላምንና ደኀንነትን የሚያስጠብቁ አካሄዶችን በመፈተሽና በትብብር መሥራትን ያረጋግጣል። ይህ ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ዘላቂ በሆነ መንገድ የሚያስቀጥልና የሚያጠናክር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በኢትዮጵያ እና ቻይና መካከል ያለው በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ሀገራቱን አስተማማኝ የልማት አጋሮች አድርጓቸዋል
May 11, 2026 222
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እና ቻይና መካከል ያለው በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ሀገራቱን አስተማማኝ የልማት አጋሮች እንዳደረጋቸው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቻይና ሕዝብ ብሔራዊ ኮንግረንስ የልዑክ ቡድን አባላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ ኢትዮጵያ እና ቻይና እ.አ.አ ከ2023 ጀምሮ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን በሁኔታዎች ወደማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነት አሳድገዋል፡፡ ሁለቱ ሀገራት በዓለም አቀፍ የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እርስ በርስ በመደጋገፍ ግማሽ ክፍለ ዘመን የተሻገረ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሥርተዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲን ትደግፋለች፡፡ የአፍሪካ ሀገራትን ተጠቃሚ በሚያደርገው የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር ዝርጋታን ጨምሮ በተለያዩ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች ተጠቃሚ መሆኗን ገልጸዋል፡፡ ቻይና የኢትዮጵያ አስተማማኝ አጋር መሆኗን ገልጸው፤ የኢትዮጵያ የግብርና፣ ማዕድን፣ የጨርቃጨርቅና ሌሎች ምርቶች ቀዳሚ ተቀባይ ሀገር ሆናለች ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የቻይና ኩባንያዎች የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት አምስት ቢሊየን ዶላር መድረሱን በመጥቀስ፤ ከሁለት ሺህ በሚልቁ ፕሮጀክቶች ከ560 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል፡፡ በደቡብ ደቡብ እና በቻይና-አፍሪካ ማዕቀፍ የሁለቱ ሀገራት ትብብር ጠንካራ መሰረት ያለው መሆኑን በመግለጽ፤ ኢትዮጵያ ለውጭ ኢንቨስትመንት ትርጉም ያለው የቢዝነስ ከባቢ ፈጥራለች ብለዋል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ትብብር እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ በበርካታ ዘርፎች የትብብር ስምምነቶችን በመፈራረም በተግባር የሚገለጽ ውጤት ማስመዝገባቸውን አንስተዋል፡፡ የሁለቱ ሀገራት የሕግ አውጪዎች የውይይትና የልምድ ልውውጥ መድረክ የሕዝብ ለሕዝብና የተቋማት ትብብርን ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን እምቅ የባህልና የቅርስ ሀብት ለቱሪዝም ልማት ማዋል እንዲችሉ በትብብር እንሰራለን ብለዋል፡፡ የቻይና ብሔራዊ ኮንግረንስ የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ባህልና የማህበረሰብ ጤና ኮሚቴ ሊቀ መንበርና የልዑኩ መሪ ሉ ሹጋንግ ወደ ኢትዮጵያና ውቧ አዲስ አበባ ለጉብኝት በመምጣታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና ቻይና በባህል፣ ቅርስና በቱሪዝም ሀብት የታደሉ ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የሁለቱ ሀገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እየተጠናከረ መጥቷል ነው ያሉት፡፡ በሁለቱ ሀገራት ምክር ቤቶች መካከል የሚደረገው እውነተኛ ትብብር በማንኛውም ጊዜ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ እና ቻይና የረጅም ጊዜ ትብብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ አመራር ሰጪነት በሁኔታዎች ወደማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማደጉን አውስተዋል። ሀገራቱ በዓለም አቀፍ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እርስ በርስ እንደሚደጋገፉ በማንሳት፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸው አድማሱን እያሰፋ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ ቻይና የተፈረሙ ስምምነቶች በፍጥነት እንዲተገበሩ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸው፤ የሀገራቱ ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክር ቤቶቹም በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ናቸው ብለዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት፣ ስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ ዘርፎች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ላለው በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂያዊ አጋርነት ትልቅ ዋጋ እንደሚሰጡ በማንሳት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ዓመታት በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ሪፎርም ማድረጓን ለቻይና ልዑክ አብራርተዋል፡፡ በሪፎርሙ የመንግስትን አገልግሎት በዲጂታል የታገዘ በማድረግ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን መልካም አስተዳደርን የማስፈን ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል፡፡ የፖለቲካ ሪፎርሙ ሰላማዊ ትብብርና ተሳትፎን የሚያረጋግጥ ምህዳር በመፍጠር የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አሳድጓል ብለዋል፡፡
በፓርቲው መሪነት ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
May 11, 2026 212
ባህርዳር፣ደሴ፣ገንዳ ውሃ ፤ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፡- በብልፅግና ፓርቲ መሪነት ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። የብልፅግና ፓርቲ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ የምርጫ ማኒፌስቶውንና የዕጩዎች ትውውቅ መድረኩን በባህርዳር፣ ደሴና ገንዳ ውሃ ከተሞች አካሂዷል። በብልጽግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በፓርቲው መሪነት በከተማዋ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የተለያዩ የልማት ስራዎች ተካሂደዋል ። የጣና ዳር አረንጓዴ ልማትና የኮሪደር ልማት፤ የአባይ ድልድይ እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ የአስፋልት መንገዶችና ሌሎች የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ከተማዋን ለቱሪዝም፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ማድረግ መቻሉን አመልክተዋል። ፓርቲው በቀጣይም መሰል የልማት ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። በተያያዘ ዜና በብልጽግና ፓርቲ የደሴ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁ በመድረኩ እንደገለፁት፣ የብልጽግና ፓርቲ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። የልማት ፕሮጀክቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የምርጫውን ሰላማዊነት ማረጋገጥ ላይ በማተኮር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የደሴ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፣ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ዳር ለማድረስ እንደሚሰራ ተናግረዋል። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የአስተዳደር ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጥላሁን መኳንንት በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ እንደገለጹት ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ክትትልና ድጋፍ እያደረገ ነው። ምርጫው የህዝብ ድምፅ የሚከበርበትና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ብልጽግና ፓርቲ በመደመር እሳቤ በሰው ተኮር የልማት ሥራዎች ውጤት አስመዝግቧል
May 11, 2026 328
ሳጃ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ብልጽግና ፓርቲ በመደመር መንግስት እሳቤ ጠንካራ ተቋማት በመገንባትና በሰው ተኮር የልማት ሥራዎች ውጤት ማስመዝገቡን በፓርቲው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገለጸ። ፓርቲው "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ አባላቱና ደጋፊዎቹ በተገኙበት ዛሬ በየም ዞን ሳጃ ከተማ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል። በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፓርቲው በለውጡ ዓመታት ባከናወናቸው ተግባራት ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ሰጥቷል። በመደመር መንግስት እሳቤ በመመራት ጠንካራ ተቋማትን ከመገንባት ባለፈ የተለያዩ ሰው ተኮር የልማት ሥራዎችን አከናውኗል ብለዋል። ብልጽግና ፓርቲ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ አበክሮ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሺመልስ እጅጉ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ዞኑ በለውጡ ዓመታት የአካባቢውን ጸጋዎች ከሰው ኃይል ልማት ጋር አቀናጅቶ ባከናወናቸው የልማት ሥራዎች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። በዚህም በመሰረተ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት እና በአትክልት ልማት ከመቼውም ጊዜ በላይ ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር ላቀዳቸው የልማት ግቦች መሳካት ህዝቡ ከፓርቲው ጎን በመሰለፍ በጠቅላላ ምርጫው ይሁንታውን እንዲሰጠውም ጥሪ አቅርበዋል። በምርጫ ቅስቀሳው ከተሳተፉት መካከል አቶ ንጉሴ ራያ እና የደሪ ዙርያ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ብርቱካን ሙራስ እንዳሉት፤ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች በተሰሩ ሥራዎች የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ መጥቷል። የብዙ ጊዜ ጥያቄያቸው የነበረው የዞን መዋቅር ምላሽ ማግኘቱን የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ በአካባቢው ስንዴ፣ አትክልትና ፍራፍሬ በስፋት በማምረት ኢኮኖሚያዊ እድገት እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል ። በተለይም በሳጃ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር፣ የመንገድ፣ የወጣቶች መዝናኛ እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ለማስቀጠል ከፓርቲው ጎን በመሆን እንደሚንቀሳቀሱም አረጋግጠዋል።
በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ ናቸው
May 11, 2026 221
ቦንጋ፤ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤቶች በብልፅግና ፓርቲ ከቀረቡ ዕጩዎች ጋር የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ በብልጽግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ ፍትሀዊ የልማት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በተሰራው የተቀናጀ ስራ ስኬት መመዝገቡን ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን ለይቶ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን አመልክተዋል። የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እንዲበቁ ከማድረግም ባለፈ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በመጀመር ሰፊ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም በመንገድ፣በድልድይና በሌሎችም መሰረተ ልማቶች ውጤት መመዝገቡን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ዘርፍ በትምህርትና በጤና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ተናግረዋል። መድረኩ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሀዊና ተዓማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ተልዕኮዎቹን ለማላቅና የጋራ ዓላማ ለመያዝም የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል። በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፥ ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ትልልቅ ሀገራዊ ተልዕኮዎችን ሲያስፈፅምና ሲፈፅም መቆየቱን ገልፀዋል። ለውጡን ለማስረፅና ለማፅናት እንዲሁም የብልፅግና ጉዞን ለማሳለጥ ርብርብ ሲደረግ ቆይቷል ያሉት አቶ ፍቅሬ፥ በሂደቱም በርካታ ሪፎርሞችን በመተግበር ውጤታማ መሆን ተችሏል ብለዋል። የክልሉ ሕዝቦች የዘመናት ጥያቄ ሆኖ የቆየው በክልል መደራጀት ምላሽ ካገኘበት ማግስት ጀምሮ በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በተመዘገቡ ውጤቶች የህዝቡ ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መምጣቱንም ተናግረዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ዲሞክራሲያዊና ፍትሃዊ እንዲሆን በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በመድረኩ ባለፉት አምስት ዓመታት በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች የተሰሩ ስራዎችና የተመዘገቡ ውጤቶች ላይ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።
ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላችንን እየተወጣን ነው- ተፎካካሪ ፓርቲዎች
May 11, 2026 212
ደሴ ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተፎካካሪ ፓርቲዎች ገለፁ። ጠቅላላ ምርጫው የህዝብ ተሳትፎ የተረጋገጠበትና ፍትሀዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ለአባላትና ለደጋፊዎቻቸው ግንዛቤ ከመፍጠር ባለፈ የምርጫ ህጉን ተከትለው እንዲሰሩ ማድረጋቸውን ፓርቲዎቹ ገልጸዋል። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ያላቸውን የፖሊሲ አማራጮች ከማስተዋወቅ ባለፈ ዴሞክራሲያዊ ሥርአቱ እየጎለበተ እንዲመጣ ለሀሳብ የበላይነት እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲ ፓርቲ የምርጫና ዴሞክራሲ ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ የሺበር ጌጡ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲውን አማራጭ ሀሳብ ለህዝብ እያስተዋወቁ ነው። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅትም ሆነ በምርጫው እለት አባሎቻቸውም ሆኑ ደጋፊዎቻቸው የምርጫ ህግን እንዲከተሉ በማድረግ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና አሳታፊነት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለፖለቲካ ፓርቲዎች የተፈጠረው ምቹ ምህዳር ህብረተሰቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የፖሊሲ አማራጭና ራዕይ ተረድቶ የሚፈልገውን ፓርቲ መምረጥ የሚችልበት አውድ ለመፍጠር ማስቻሉንም ገልጸዋል። "የሰላም ለኢትየጵያ ጥምር ፓርቲ" የምርጫና የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊና የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ፕሬዚዳንት አቶ አላምረው ይርዳው እንዳሉት፤ በጠቅላላ ምርጫው ፓርቲያቸው ሰላምና ልማትን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለህዝብ በተለያየ መንገድ አስተዋውቋል። በምርጫው ጠንካራ ፉክክርና ክርክር ከማድረግ ባለፈ ተዓማኒ፣ ሰላማዊና አሳታፊ እንዲሆን አበክረው እየሰሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ምርጫ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት አንዱና ወሳኝ በመሆኑ በሀሳብ የበላይነት ለማሸነፍ እየተወዳደሩ መሆናቸውን ያነሱት ደግሞ የአንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የቦርድ አባል አቶ ዮሴፍ አሻግሬ ናቸው። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን አባሎቻቸውና ደጋፊዎቻቸው የድርሻቸውን እንዲወጡ የማስገንዝብ ሥራ መስራታቸውን ገልጸዋል፡፡
ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችንን እንወጣለን- የምስራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች ክልሎች ሴቶች
May 10, 2026 433
ድሬደዋ ፣ ግንቦት 2/2018(ኢዜአ):- የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ የምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎች ሴቶች አስታወቁ። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን ለምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎች ሴቶች በድሬደዋ ያዘጋጀው የምርጫ ታዛቢነት የአሰልጣኞች ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል። በስልጠናው ላይ የተሳተፉት የድሬደዋ አስተዳደር፣ የሐረሪ እና የሶማሌ ክልሎች ሴቶች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ለሁለት ቀናት የተሰጣቸው ስልጠና በዘንድሮ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ የተጣለባቸው የታዛቢነት ኃላፊነት በላቀ ብቃት ለመወጣት ያስችላቸዋል። ከሶማሌ ክልል ጅግጅጋ የተሳተፉት ወይዘሮ ከድራ ኢብራሂም እንደተናገሩት፤ የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ታአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በትኩረት እየሰሩ ናቸው። በተለይም በምርጫው የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና የውሳኔ ሰጪነት ሚና እንዲጎለብት እየሰሩ መሆኑን በመግለፅ። ለሁለት ቀናት የተሰጠን የምርጫ ታዛቢነት የአሰልጣኞች ስልጠና በምርጫው ያለብንን ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት ያስችለናል ያሉት ደግሞ ከሐረሪ ክልል ሴቶች ፌደሬሽን የተሳተፉት ወይዘሮ ነጃሃ ኡመር ናቸው። የቀሰምነውን ዕውቀት በየክልሎቻችን ለሚገኙ የምርጫ ታዛቢ ሴቶች በማካፈል በጠቅላላው ምርጫ ህግና ደንብ በአግባቡ እንዲተገበር የድርሻችንን ኃላፊነት ለመወጣት ያስችለናል ብለዋል። ከድሬደዋ አስተዳደር የሴቶች ፌዴሬሽን የተሳተፉት ወይዘሮ ቅድስት አየለ በበኩላቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች በመራጭነት፣ በተመራጭነት እና በታዛቢነት በመሳተፍ ምርጫው በህዝብ ዘንድ ቅቡል እና ፍፁም ታአማኒ ሆኖ እንዲካሄድ የተቀናጀ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል። በአስተዳደሩ በምርጫ ታዛቢነት የሚሳተፉ ሴቶች የታዛቢነት መብትና ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲገነዘቡ መደረጉ ኃላፊነትን በትክክል ለመወጣት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል ። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ትዕግሥት ተረፈ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና የውሳኔ ሰጪነት ሚና እንዲጎለብት ውጤታማ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። ፌዴሬሽኑ በሀገሪቱ በሁሉም አቅጣጫዎች የሚገኙ ሴቶች በሁሉም መስክ ተሳትፏቸው እንዲጨምር መስራቱን ጠቅሰው በፌዴሬሽኑ በ54 የተለያዩ አደረጃጀቶች የታቀፉ ሴቶች አባላቱ በምርጫው የላቀ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን አንስተዋል። በዘንድሮ ምርጫ ላይ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ 10 ሺህ ሴቶች ነፃ እና ገለልተኛ ሆነው በታዛቢነት ይሳተፋሉ ብለዋል።
ፓርቲው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በማስቀጠል የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበልጥ ይሰራል
May 10, 2026 411
ገንዳውኃ/ደብረ ብርሃን ፤ግንቦት 2/2018(ኢዜአ)፡- የብልጽግና ፓርቲ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በማስቀጠል የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበልጥ እንደሚሰራ አስታወቀ። የብልጽግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ በምዕራብ ጎንደር ዞንና ደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ ዛሬ አካሂደዋል። የምእራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ ባስተላለፉት መልእክት እንደገለጹት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ለማስቀጠል ሰላማዊና ፍትሃዊ ምርጫን ማካሄድ ተገቢ ነው። ብልጽግና ፓርቲም ይህንኑ ለመተግበር ለአባላትና ለደጋፊዎቹ ጭምር የምርጫ ስነምግባር ማስተማሩን ተናግረዋል። በሰልፉ ላይ የተገኙት የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪ አቶ እንዳላማው ማሩ በበኩላቸው በከተማዋ የተከናወኑ የኮሪደር፣ የመንገድ፣ የወጣቶች መዝናኛና የስፖርት ማዘውተሪያ እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል። ይህን ለማስቀጠል የሚሆነን ፓርቲ መምረጥ ይገባናል ብለዋል። በተያያዘ ዜና በደብረ ብርሃን ከተማ በተካሄደው የምርጫ ቅስቀሳ መልእክት ያስተላለፉት የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት እንደ ሀገር የተፈጠረው አካታች የፖለቲካ ምህዳርን በመጠቀም የብልጽግና ፓርቲ የፖሊሲ አማራጮቹን ይዞ ቀርቧል። የተመዘገበውን ሀገራዊ እድገት ለማስቀጠል ፓርቲው ጠንክሮ እንደሚሰራም ጠቁመዋል። በከተማ አስተዳደሩ ባለፉት አምስት ዓመታት የተገኘውን እድል በማስፋት ከተማዋን የቱሪዝም፣ የኢንቨስትመንትና የንግድ ማእከል ለማድረግ የዘንድሮውን ምርጫ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር እየተሰራ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳው ከተሳተፉት መካከል አቶ ዘሪሁን ከበደና አቶ ዓለማየሁ ሸዋንግዛው እንዳሉት በብልጽግና ፓርቲ የተጀመሩ የሰላምና የልማት ትሩፋቶችን ለማስቀጠል በምርጫው በንቃት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ማህበራዊ
ለተቃና ነገ የኢትዮጵያ ትጋት አንዱ መገለጫ
May 11, 2026 402
(በዮሐንስ ደርበው) ኢትዮጵያ ከምትከውናቸው ዐበይት ጉዳዮች መካከል ሰው ተኮር ተግባራት ቀዳሚው ነው። በአዲስ አበባ በተካሄደው ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ጥረት ሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ ነው ብለዋል። መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል አድርጎ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በዚህም መሠረት፤ የልጆች ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት፣ የምገባ ሥርዓትን ማሳደግ፣ የሕጻናት መጫወቻ ሥፍራዎች ግንባታ ላይ ተጨባጭ ውጤቶች መምጣታቸውንም ነበር የጠቀሱት። ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማትና ትምህርት ፖሊሲ የዘላቂ ብልጽግና መንገዳችን ከሆነው የመደመር ዕሳቤ ጋር በተናበበ መልኩ እየተተገበረ በስኬት ቀጥሏልም ብለዋል። ኢትዮጵያ ለነገ የተዘጋጀ ትውልድ ለመገንባት በሕግና በፖሊሲ የተደገፉ የቀዳማይ ልጅነት ኢኒሼቲቮችን እየተገበረች እንደምትገኝም አስታውቀዋል። ለአብነትም፤ በ2015 ተሻሽሎ የፀደቀው ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማት እና ትምህርት የፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲሁም በ2017 የፀደቀውን አጠቃላይ የትምህርት አዋጅ መሠረት በማድረግ ከ35ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላው ሀገሪቱ እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል። በመንግሥት ተቋማት የሕጻናት ማቆያ ማዕከላት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በመጠቆምም፤ ኢትዮጵያ የሕጻናትን ደኅንነት ማሻሻል የሚያስችል ጉልኅ ብሔራዊ መርሐ-ግብር መጀመሯን አንስተዋል። በሰቆጣ ቃል ኪዳን አማካኝነት የ15 ዓመት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ ከሁለት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ላይ የሚደርሰውን መቀንጨር በ2022ዓ.ም ዜሮ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። የሌማት ትሩፋትና የአልሚ ምግቦች ምርታማነት የሕጻናትን ጉዳት ለመቀነስና የልጆችን ጤናማነት መጨመር እያስቻሉ እንደሚገኙም ነው የተናገሩት። ኢትዮጵያ ለዘላቂ የልማት ግቦችና ለሕጻናት መብቶች ጥበቃ የገባቻቸውን ቃል ኪዳኖች ወደ ተግባር እየለወጠች መሆኑን በማንሳት፤ ይህንንም አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። መንግሥት ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን በመላ ሀገሪቱ ለማስፋት ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑንም አመላክተዋል። በዚህም መሠረት፤ በጀት በመመደብ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል፣ የተማሪዎችን ምገባ በማስፋፋት ውጤት ማምጣቱን ነው የሚያብራሩት። ልጆች በአካልና በመንፈስ የሚጎለብቱባቸው የስፖርትና የመዝናኛ ቦታዎች በየአካባቢው በመገንባት፣ በኮሪደር ልማት ለልጆች ምቹ ሥፍራ እየተፈጠረ መሆኑንም በመጥቀስ። ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር፣ አኅጉር እና ዓለም ላይ መሥራት በመሆኑ በትጋት ማስቀጠል እንደሚገባም በአጽንኦት ይናገራሉ። አፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ተግዳሮቶችን ለመፍታት የራሷን መፍትሔዎች በማፍለቅ፣ በብሔራዊ የልማት አጀንዳዋ እያካተተች መሆኑን የሚገልጹት ደግሞ የአፍሪካ ቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ከበደ ወርቁ ናቸው። በሕጻናት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ማንኛውም ሀገር በመጪው ትውልድ ላይ ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው እጅግ አስፈላጊ ኢንቨስትመንቶች አንዱ መሆኑንም ያነሳሉ። አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ ያሉባትን ተግዳሮቶች ከመጋፈጥ ባለፈ፤ የራሷን መፍትሔዎች እያመነጨች መሆኑንና ጉዳዩን የብሔራዊ ልማት አጀንዳዋ አካል እያደረገችው እንደምትገኝም ገልጸዋል። አዲስ አበባ ይህን ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ እንድታስተናግድ የተመረጠችበት ዋና ምክንያትም፤ በዘርፉ እያከናወነች ያለው ተግባር አርዓያነት ያለው በመሆኑ ነው ብለዋል። ከተማዋ የጤና እና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎቶችን ያካተተ የተቀናጀ ዘርፈ-ብዙ አሠራር መዘርጋቷን ጠቅሰው፤ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት እና የቀን የሕጻናት እንክብካቤ ማዕከላትን በከተማ አቀፍ ስትራቴጂ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝም ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው፤ መዲናዋ በቀዳማይ ልጅነት ያመጣችው ተጨባጭ ውጤት በአርዓያነት እንድትጠቀስ እንዳደረጋት አንስተዋል። በሕጻናት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች፤ በትምህርት፣ በሰው ሃብት ልማትና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ፋይዳ እንዳለውም አስረድተዋል። በዚህም በአዲስ አበባ ፍትሐዊና አካታች የቀዳማይ ልጅነት ልማት መርሐ-ግብርን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ የትውልድ ግንባታ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል። "ሕጻናት የአዲስ አበባ የነገ ተስፋዎች" የሚል ፍኖተ ካርታ በመቅረጽ 1 ነጥብ 3 ሚሊየን ለሚሆኑ ከስድስት ዓመት በታች ሕጻናት ሁለንተናዊ ዕድገት መረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በትምህርት ቤት ምገባ መርሐ-ግብርም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ ዩኒፎርምና በቀን ሁለት ጊዜ ምግብ በማቅረብ በሕጻናት ክብካቤ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል ነው ያሉት። የሕጻናት ማቆያና መጫወቻ የመሠረተ-ልማት ግንባታ፤ ሕጻናት ነፃ የሕክምና፣ የምገባና የሥነ-ልቦና አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። የቀዳማይ ልጅነት መርሐ-ግብር በ2015 ዓ.ም ሲጀመር በዕድገት ወደ ኋላ የቀሩ የሕጻናት መጠን ከነበሩበት 13 በመቶ አሁን ላይ ወደ 10 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉን ከንቲባዋ አመላክተዋል። አክለውም፤ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዝግጁነታቸው ከነበረበት 49 በመቶ አሁን ወደ 90 በመቶ ማደጉንም ተናግረዋል። ሀገር በሁሉም ዘርፍ የበቃ መጪ ትውልድ እንዲኖራት መንግስት የያዘው ጥረት በሚፈለገው መጠን ለውጤት እንዲበቃ የሁሉንም ትኩረትና ተሳትፎ ይሻል። ለነገ በሁሉም ዘርፍ የዳበረ ትውልድና የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን ዛሬ ላይ እየተደረገ ያለው ርብርብ የሀገራችንን መፃኢ ብሩህ ተስፋ ይበልጥ የሚያለመልም ነውና ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
የቀዳማይ ልጅነት የልማት መርሃ ግብር አዲስ አበባን አፍሪካዊት የትውልድ ግንባታ ተምሳሌት ከተማ እያደረጋት ነው
May 11, 2026 223
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦የቀዳማይ ልጅነት የልማት መርሃ ግብር አዲስ አበባን አፍሪካዊት የትውልድ ግንባታ ተምሳሌት ከተማ እያደረጋት መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ''አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ሥርዓት ለውጥ የግንባር ቀደምትነት ሚና፤ ከአካባቢያዊ ሞዴሎች ወደዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ” በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀውን አዲስ ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤን በይፋ ከፍተዋል። በዚሁ ወቅት የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ መዲናዋ በቀዳማይ ልጅነት ያመጣችው ተጨባጭ ውጤት በአርዓያነት እንድትጠቀስ አድርጓታል ብለዋል። ከፅንስ እስከ ስድስት ዓመት የዕድሜ ክልል የሚደረግ ስኬታማ ኢንቨስትመንት አዲስ አበባን የአፍሪካ ተመራጭ የህፃናት ማሳደጊያ ከተማ እያደረጋት መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ለሕፃናትና እናቶች ምቹ ምኅዳር መፍጠር ለቤተሰብ፣ ማህበረሰብና ለሀገር ዘላቂ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ተናግረዋል። በሕፃናት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች በትምህርት፣ በሰው ሃብት ልማትና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰዋል። በዚህም በአዲስ አበባ ፍትሐዊና አካታች የቀዳማይ ልጅነት የልማት መርሃ ግብርን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ የትውልድ ግንባታ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል። "ሕፃናት የአዲስ አበባ፤ የነገ ተስፋዎች" የሚል ፍኖተ ካርታ በመቅረፅ 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ለሚሆኑ ከስድስት ዓመት በታች ሕፃናት ሁለንተናዊ ዕድገት መረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። ፍኖተ ካርታውም የተቋማትን ቅንጅት በማሰናሰል የተቀናጀ የቀዳማይ ልጅነት ልማት አገልግሎት በሁሉም የመንግስት ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች በመደበኛነት እንዲሰጥ አስችሏል ብለዋል። በትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብርም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ ዩኒፎርምና በቀን ሁለት ጊዜ ምግብ በማቅረብ በሕጻናት ክብካቤ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል። የሕፃናት ማቆያና መጫወቻ የመሰረተ ልማት ግንባታ ውጤቶችም ሕፃናት ነፃ የሕክምና፣ የምገባና የሥነ-ልቦና አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። የቀዳማይ ልጅነት መርሃ ግብር በ2015 ዓ.ም ሲጀመር በዕድገት ወደ ኋላ የቀሩ የሕፃናት መጠንን ከነበረበት 13 በመቶ አሁን ላይ ወደ 10 ነጥብ 9 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል። የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዝግጁነታቸው ከነበረበት 49 በመቶ አሁን ላይ ወደ 90 በመቶ ማሳደግ እንደተቻለም አስታውቀዋል።
አፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ተግዳሮቶችን ለመፍታት የራሷን መፍትሄዎች በማፍለቅ በብሔራዊ የልማት አጀንዳዋ እያካተተች ትገኛለች
May 11, 2026 181
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦አፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ተግዳሮቶችን ለመፍታት የራሷን መፍትሄዎች በማፍለቅ፣ በብሔራዊ የልማት አጀንዳዋ እያካተተች መሆኑን የአፍሪካ ቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ከበደ ወርቁ ገለጹ። አዲስ ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ “አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ሥርዓት ለውጥ የግንባር ቀደምትነት ሚና፤ ከአካባቢያዊ ሞዴሎች ወደ ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ” በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የማዕከሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ከበደ ወርቁ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ በታዳጊ ሕፃናት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ማንኛውም ሀገር በመጪው ትውልድ ላይ ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው እጅግ አስፈላጊ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ነው። አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ ያሉባትን ተግዳሮቶች ከመጋፈጥ ባለፈ የራሷን መፍትሄዎች እያመነጨች መሆኑንና ጉዳዩን የብሔራዊ ልማት አጀንዳዋ አካል እያደረገችው መሆኑንም ጠቁመዋል። አዲስ አበባ ይህንን ጉባኤ እንድታስተናግድ የተመረጠችበት ዋና ምክንያት፣ በዘርፉ እያከናወነች ያለው ተግባር አርአያነት ያለው በመሆኑ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ከተማዋ የጤና እና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎቶችን ያካተተ የተቀናጀ ዘርፈ-ብዙ አሠራር መዘርጋቷን ጠቅሰው፤ የቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት እና የቀን የሕፃናት እንክብካቤ ማዕከላትን በከተማ አቀፍ ስትራቴጂ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝም አስረድተዋል። በተጨማሪም ለሕፃናት ተስማሚ የሆኑ የመጫወቻ ቦታዎችን እና የወላጆች ድጋፍ ፕሮግራሞችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። የፖለቲካ አመራር ቁርጠኝነት፣ በማስረጃ ላይ የተመሠረተ የውሳኔ አሰጣጥ፣ የፖሊሲ ትግበራ፣ የሰው ኃይል ግንባታ እንዲሁም ለዘላቂ ሥርዓት የሚውል ፋይናንስና ኢንቨስትመንት የጉባኤው ዋነኛ አጀንዳዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል። ጉባኤው በተግባራዊ ትምህርት፣ በጠንካራ አጋርነት እና በመንግሥታት መካከል በሚደረግ የልምድ ልውውጥ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግም አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ለነገ የተዘጋጀ ትውልድ ለመገንባት በሕግና በፖሊሲ የተደገፉ የቀዳማይ ልጅነት ኢኒሼቲቮችን እየተገበረች ትገኛለች
May 11, 2026 169
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለነገ የተዘጋጀ ትውልድ ለመገንባት በሕግና በፖሊሲ የተደገፉ የቀዳማይ ልጅነት ኢኒሼቲቮችን እየተገበረች እንደምትገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤን በይፋ ከፍተዋል። ኢትዮጵያ በሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ከምትተገብራቸው ሥራዎች መካከል የቀዳማይ ልጅነት መርኃ ግብር አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥት ለሕፃናት ሁለንተናዊ ዕድገት እና ጥበቃ በሕግና በፖሊሲ የተደገፉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በ2015 ተሻሽሎ የፀደቀው ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማት እና ትምህርት የፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲሁም በ2017 የጸደቀውን አጠቃላይ የትምህርት አዋጅ መሠረት በማድረግ ከሠላሳ አምስት ሺህ በላይ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላው ሀገሪቱ እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል። በመንግሥት ተቋማት የሕጻናት ማቆያ ማዕከላት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ የሕፃናትን ደኅንነት ለማሻሻል የሚያስችል ጉልህ ብሔራዊ መርሐ ግብር መጀመሯን አንስተዋል። በሰቆጣ ቃል ኪዳን አማካኝነት የዐሥራ አምስት ዓመት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ ከሁለት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ላይ የሚደርሰውን መቀንጨር በ2022 ዓ.ም ዜሮ ለማድረግ እየተሠራ ሲሆን የሌማት ትሩፋትና የአልሚ ምግቦች ምርታማነት ለስኬቱ ሚናቸው የላቀ ነው ብለዋል። በተለይም የሕጻናትን ጉዳት ለመቀነስና የልጆችን ጤናማነት ለመጨመር እያስቻሉ እንደሚገኙ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ለዘላቂ የልማት ግቦች እና ለሕጻናት መብቶች ጥበቃ የገባቻቸውን ቃል ኪዳኖች ወደ ተግባር እየለወጠች መሆኑን በማንሳት፤ ይህንንም አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ አመራሩ በወሰደው ቁርጠኝነት፣ በሕፃናት ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ ያተኮሩ ስትራቴጂያዊ ኢኒሼቲቮች ተቀርፀው በተግባር ላይ እየዋሉ እንደሚገኙም አስረድተዋል። ይሕ ወሳኝ የትውልድ ግንባታ ሥራ በአዲስ አበባ ከተማ ፋና ወጊነት ተጀምሮ በመላ ሀገሪቱ እየተስፋፋ መሆኑንም ጠቁመዋል። መንግሥት ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን በመላ ሀገሪቱ ለማስፋት ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑንም አረጋግጠዋል። አስፈላጊውን በጀት በመመደብ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል፣ የተማሪዎችን ምገባ በማስፋፋት ረገድ ውጤት ማምጣቱንም ጠቅሰዋል። ልጆች በአካልና በመንፈስ የሚጎለብቱባቸው የስፖርትና የመዝናኛ ቦታዎች በየአካባቢው በመገንባት፣ በኮሪደር ልማት ለልጆች ምቹ ሥፍራ እየተፈጠረ መሆኑንም ጠቁመዋል። ልጆች ላይ መሥራት ማለት በነገ ሀገር፣ አህጉር እና ዓለማችን ላይ መሥራት በመሆኑ በትጋት ማስቀጠል ይገባል ነው ያሉት።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አሠራሩን ለማዘመንና ተወዳዳሪ ለመሆን እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ ነው
May 11, 2026 185
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አሰራሩን በማዘመን ከወቅቱ ጋር ለመዘመንና ተወዳዳሪ ለመሆን እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ። ቋሚ ኮሚቴው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የበጀት አፈፃፀምንና የ2019 በጀት ዓመት እቅድን ገምግሟል። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አመራሮች እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ላለፉት 85 ዓመታት የኢትዮጵያን ታሪክ በጽሑፍም በፎቶ ግራፍም ሰንዶ የያዘ አንጋፋ ተቋም ነው፡፡ በድርጅቱ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኤፍሬም ተክሌ፤ በአሁኑ ወቅት ዲጂታል ሚዲያው ለህትመት ሚዲያው ፈታኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። ድርጅቱም የዲጂታል ሚዲያውን መስፋፋት ታሳቢ አድርጎ እዩሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በህትመትም በዲጂታልም ተወዳዳሪና ተደራሽ ለመሆን ለዲጂታል አሰራሮች ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል፡፡ የድርጅቱ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወንድም ተክሉ በበኩላቸው፤ ድርጅቱ የራሱ የጋዜጣ እና መጽሔት ህትመት ቤት አለመኖሩ ለሥራው ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነበት ተናግረዋል፡፡ ይህ በተደጋጋሚ ሲነሳ የቆየ ችግር መሆኑን አንስተው፤ የጋዜጣና የመፅሔት ህትመት የየራሳቸው ባህሪ፣ ጥራትና ደረጃ የሚጠይቁ በመሆናቸው በተለያዩ ማተሚያ ቤቶች ለማሳተም እንደሚገደድ ጠቁመዋል። ለሁለቱም ህትመቶች የሚሆኑ ማተሚያ ቤቶች እንዲኖረው ቢደረግ የድርጅቱን አሠራር እንደሚያሻሽልና ወጪን እንደሚቀንስ ጠቅሰዋል። ከዚህም ባለፈ ለሌሎች ድርጅቶች ጭምር የህትመት አገልግሎት በመስጠት የገቢ ምንጭ ማድረግ እንደሚችልም አንስተዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ብዝኃነትን መሰረት ያደረገ የህትመት አቅምን ለማሳደግ እያደረገ ያለውን የሪፎም ሥራ አድንቀዋል። ድርጅቱ ከወቅቱ ጋር ለመዘመንና ተወዳዳሪ ለመሆን እያደረገ ያለው ተግባር የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ብለዋል። የድርጅቱ ማተሚያ ቤት ጥያቄ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ምክክር እንደሚደረግበትና እንደሚታይ ጠቁመዋል። ተቋሙ አሠራሩን ለማሻሻልና የገቢ አቅሙን ለማሳደግ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው
May 11, 2026 140
ሀዋሳ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን የበቆሎ ማሳ በመስክ ተመልክተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅት ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብዓቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። በክልሉ ያለውን የእርሻ አቅም አሟጦ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና በምግብ ራስን የመቻል ግብን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶች ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመው ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በበልግ ወቅት በክልሉ በሰብል የሚለማ የመሬት መጠን እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ አብዛኛው መሬት በምርጥ ዘር መሸፈኑን ተናግረዋል። የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ በበልግ እርሻ ከ152 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ዋና ዋና ሰብሎች እንዲሁም በስራስርና አትክልቶች መሸፈኑን ተናግረዋል። አጠቃላይ ከለማው መሬትም ከ24 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል። በልማቱ እየተሳተፉ ካሉ መካከል በሎካ አባያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ጽጌ ኩማ እንደገለጹት የአካባቢው 80 አርሶ አደሮች ከ75 ሄክታር በላይ ኩታ ገጠም መሬት ላይ በቆሎ እያለሙ መሆናቸውንና የማሳ እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሌላው በዳራራ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ዳዊት ብንኦ 40 ሆነው በኩታገጠም በቆሎ እያለሙ መሆናቸውን ጠቁመው ምርቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና በጋራ መስራታቸው ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በልማት ዘርፎች የጀመረቻቸው ግዙፍ ተግባራት ቃል በተግባር የተፈጸመባቸው ድሎች ናቸው -የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
May 11, 2026 189
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በተለያዩ የልማት ዘርፎች የጀመረቻቸው ግዙፍ ተግባራት የትውልድ ተስፋ ከመሆን ባለፈ፣ በተጨባጭ ስኬቶች የታጀቡና ቃል በተግባር የተፈጸመባቸው ድሎች መሆናቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። በግብርናው ዘርፍ፣ በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው ዐቢይ ለውጥ ሀገሪቱን ከውጪ የዕርዳታ ስንዴ ጥገኝነት አላቆ ራስን ወደ መቻል ከፍ ማድረጉንም ገልጿል። ምርቱን ለውጭ ገበያ ማቅረብ (ኤክስፖርት) መጀመሩም፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ትግል ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩን ጠቁሟል። በኢንዱስትሪው መስክ የውጭ ምንዛሬ ፍሰትን ለመታደግ የተወጠነው "የተኪ ምርቶች ንቅናቄ"፣ የኢንዱስትሪ ግብአቶችንና የፍጆታ ዕቃዎችን በሀገር ውስጥ በማምረት ረገድ ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ እንደሚገኝ አገልግሎቱ አመልክቷል። ይህም ሀገራዊ ምርታማነትን በማነቃቃት የኢኮኖሚውን መዋቅር እያጠናከረ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥቷል። የከተሞችን ገጽታ ለማሻሻልና ለዜጎች ክብር ያለው ሕይወት ለመስጠት የተጀመረው የኮሪደር ልማት፣ አዲስ አበባንና የክልል ከተሞችን የኮንፈረንስ ቱሪዝም መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ መሠረተ ልማቶችን እውን በማድረግ ዜጎች በሀገራቸው አዲስ ተስፋ እንዲሰንቁ ማድረጉን አገልግሎቱ አውስቷል። የኢትዮጵያዊያን የጋራ ትብብር ማሳያ በሆነው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም ኢትዮጵያ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በሚደረገው ዓለም አቀፍ ጥረት ቀዳሚ ከሆኑ አገራት ተርታ እንድትሰለፍ ያደረገ የማይደበዝዝ አሻራ ማኖሯን አስገንዝቧል። ነባር የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማደስ፣ አዳዲስ መዳረሻዎችን በመገንባትና የንጹህ ኢነርጂ ኢንቨስትመንቶችን በማስፋፋት የተሰራው ወሳኝ ሥራ፣ ሀብቶች ለኢኮኖሚ መሰረት እንዲሆኑ በማስቻል ረገድ ፍሬው የሚታይበት ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደሚገኝም አስታውቋል። እነዚህ ስኬቶች የመንግሥትና የሕዝብ የጋራ ቁርጠኝነት ውጤቶች መሆናቸውን የጠቀሰው አገልግሎቱ፤ ኢትዮጵያ በትክክለኛ የልማትና የዕድገት ጎዳና ላይ መሆኗንና በዜጎች ሕይወት ላይ ተጨባጭ ለውጥ የሚመጣበት የታሪክ ምዕራፍ ላይ መደረሱን የሚያረጋገጥ እንደሆነ አገልግሎቱ በመረጃው አመልክቷል።
በከተማ አስተዳደሩ ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደዋል
May 11, 2026 142
ባህር ዳር ፤ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፡-በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ገለፀ። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመምሪያው ኃላፊ ብርሃን ንጉሴ ለኢዜአ እንዳሉት፤በከተማዋ የኢንቨስትመንት ዘርፉን በተቀናጀ አግባብ ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ ናቸው ። ባለፉት ዘጠኝ ወራትም 320 አዳዲስ ባለሃብቶች መዋለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደዋል ብለዋል። ባለሃብቶቹ ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ሲሆን ወደ ስራ ሲገቡም ከ19 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል የመፍጠር አቅም እንዳላቸው ተናግረዋል። ባለሃብቶቹ ፈጥነው ወደ ስራ እንዲገቡ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተው፤ በዚህ ዓመትም መስፈርቱን ለሚያሟሉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 102 ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን ገልፀዋል። በከተማው ቀደም ሲል የኢንቨስትመንት ቦታ ወስደው ተደጋጋሚ እገዛና ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ስራ ያልገቡ 24 ባለሃብቶችም የወሰዱትን ቦታ እንዲመልሱ መደረጉንም አስታውቀዋል። በከተማዋ በኮሪደር ልማት የተከናወኑት ተግባራት ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ተመራጭ እንድትሆን ያደረጉ ሲሆን በተለይ በአገልግሎትና ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ ምቹ ሁኔታ እንዳለ አመልክተዋል። ከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንትን ከማሳደግ ጎንለጎንም ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተካሔደ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 23 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ማድረጉን ገልፀዋል። በዚህም ከ 3 ሺህ 800 ለሚበልጡ ወገኖች የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉንም ገልፀዋል በ98 ኢንዱስትሪዎችም 155 ነጥብ 6 ቶን ተኪ ምርት በማምረት ከ118 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን እንደተቻለ አስረድተዋል። ዘጠኝ አምራች ኢንዱስትሪዎች 17 ነጥብ 7 ቶን የተለያዩ ምርቶችን ወደ ውጭ ሃገራት ገበያ በመላክ 22 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል ነው ያሉት። የኢትዮጰያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅምም ከ59 በመቶ ወደ 63 በመቶ ከፍ ማድረግ እንዳስቻለም አስገንዝበዋል። በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩ 287 ኢንዱስትሪዎች እንዳሉም የመምሪያ ኃላፊዋ ጨምረው አስታውቀዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራትን በጥናትና ምርምር ማገዝ ይገባል
May 11, 2026 149
ወራቤ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራትን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር ማገዝ እንዳለባቸው ተገለጸ። "የምርምርና የፈጠራ ሥራን ለዘላቂ ልማት ግቦች መሳካት" በሚል መሪ ሀሳብ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ በወራቤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የጥናትና ምርምር ሥራዎች ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት የሚከናወኑ ተግባራትን ስኬታማ ለማድረግ ወሳኝ መሆናቸውም ተመላክቷል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ቶፊቅ ጀማል (ዶ/ር) በዚሁ ወቀት እንዳሉት በጥናትና ምርምር የታገዘ የልማት ሥራ ቀጣይነት ላለው እድገት ወሳኝ ነው። እንደሀገር ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት በመንግስት የሚከናወኑ ተግባራትን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር በማገዝ ስኬታማ ለማድረግ መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ወራቤ ዩኒቨርሲቲ እንደሀገር ዘላቂ የልማት ግቦችን ስኬታማ ለማድረግ የሚከናወኑ ሥራዎችን በጥናትና ምርምር በማገዝ የበኩሉን ለመወጣት እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። መንግስት ለዲጂታል ቴክኖሎጂ የሰጠውን ትኩረት ለማገዝም ዩኒቨርሲቲው ከደቡብ ኮሪያው "ዮንግናም ዩኒቨርሲቲ" ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በሰው ሰራሽ አስተውሎት (አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ) ተማሪዎችን ተቀብሎ እያሰለጠነ መሆኑን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ዛሬ የተጀመረው ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስም ተሞክሮ የሚገኝበት ከመሆኑ ባለፈ በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ ያሉ የምርምር ሥራዎችን ተወዳዳሪነት ከፍ ለማድረግ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ ምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ረዳት ፕሮፌሰር አንዋር አህመድ በበኩላቸው እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በቢዝነስ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ መስኮች ላይ ያተኮሩ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። የዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንሱ በዩኒቨርሲቲው መካሄድ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን አጠናክሮ ለማስፋፋት ካለው ፋይዳ በተጨማሪ እርስ በርስ ተሞክሮ ለመለዋወጥ ያስችላል ብለዋል። በመድረኩ ተገኝተው የምርምር ሥራቸውን ያቀረቡት በጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ድልነሳው የኋላው እንደገለፁት፣ ስኬቶችን ለማጠናከርና ተግዳሮቶችን ለመፍታት በምርምርና በፈጠራ የታገዙ ሥራዎችን ማከናወን ያስፈልጋል። በአስተማማኝና ዘላቂ ኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት ውስጥ በጥናትና ምርምር የተደገፈ ሥራ ለመስራት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና የጎላ መሆኑን አስታውቀዋል። የምርምር ኮንፍረንሱ ለሀገር የሚጠቅሙ ዓለም አቀፋዊ ተሞክሮዎችን ለመቀመር እንደሚያስችል የተናገሩት ደግሞ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመጡት መምህርና ተመሪማሪ ጋዲሳ አዳሙ ናቸው። ለሦስት ቀናት በሚቆየው መድረክ ከሀገር ውስጥና ከውጪ የመጡ 43 ተመራማሪዎች የምርምር ሥራዎቻቸውን በማቅረብ የልምድ ልውውጥ እንደሚደረግ ታውቋል።
የመረጃ ሥርዓትን በማጎልበት ዲጂታል የጤና ስርዓትን ለማጠናከር የተቋማት ቅንጅታዊ አሠራር ወሳኝ ነው
May 11, 2026 216
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ የመረጃ ሥርዓትን በማጎልበት ዲጂታል የጤና ስርዓትን የበለጠ ለማጠናከር የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር እንደሚጠናከር የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። የጤና ሚኒስቴር ''በዲጂታል ጤና ፈጠራዎች ላይ ዘላቂ ኢንቨስትመንት በማድረግ የጤና ትሩፋቶችን ማሳደግ'' በሚል መሪ ሃሳብ 5ኛው ሀገር አቀፍ የጤና መረጃና ዲጂታል ጤና ሳምንት መርሃ ግብር እያካሄደ ነው። በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ የጤና ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች፣ የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲ እንዲሁም የሙያና ሲቪል ማኅበራት ተወካዮች ተገኝተዋል። የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚህ ወቅት፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትግበራ የጤና ዘርፍ የመረጃ ስርዓትን የሚያዘምን መሰረት ተጥሏል ብለዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለጤና ዲጂታል ሥርዓት መጠናከር ትኩረት መሰጠቱንና የኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓት የጤናውን ዘርፍ በማዘመን ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል። ከጤናው ዘርፍ አምስት ምሰሶዎች መካከል የመረጃ ስርዓት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው ጠንካራ የጤና መረጃና ዲጂታል ጤና ለዘርፉ አፈጻጸምና ለሕብረተሰብ ጤና መሻሻል ጉልህ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል። ሁሉን አቀፍ የጤና ስርዓት ለመዘርጋትና የጤና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዲጂታል ጤና ወሳኝ ነው ብለዋል። የዲጂታል ጤና አበረታች ውጤቶች ማስመዝገቡን ጠቁመው፤ ከ47 በላይ የዲጂታል ጤና መሳሪያዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ ሥራ ላይ እየዋሉ ነው ብለዋል። ከ3ሺህ 500 በላይ የጤና ተቋማት በኸልዝኔት(HealthNet) መገናኘታቸውንና ከ227 በላይ ተቋማት የታካሚዎችን መረጃ በኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት የማካተት ሥራ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ማደረጋቸውን አስታውቀዋል። ዩኒቨርሲቲዎች በሰው ሃብት ልማት፣ ምርምርና ፈጠራዎችን በማበረታታት ገንቢ ሚና በመወጣት የመረጃና ዲጂታል ጤና እንዲጠናከር መስራት እንዳለባቸውም ተናግረዋል። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አፀደ ወይን(ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የጤና መረጃ ስርዓት እንዲዘምን በሰው ኃይል ልማት ላይ በግንባር ቀደምትነት ሲሠራ ቆይቷል ብለዋል። የጤና መረጃ ስርዓትን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ከጤና ሚኒስቴር እና አጋር አካላት ጋር በመሆን የወረዳዎችን የመረጃ አያያዝ ማዘመን የሚያስችሉ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጀማል አባፊጣ(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው በኦሮሚያ፣ ደቡብ ምዕራብና ጋምቤላ ክልሎች ያሉ ወረዳዎችን የመረጃ አያያዝ ማዘመን የሚያስችል ድጋፍ ማድረጉን ጠቁመዋል። በዛሬው እለት ለዩኒቨርሲቲውና የአቅም ግንባታ ድጋፍ ላደረገላቸው ተቋማት የተሰጠው እውቅና ለበለጠ ሥራ የሚያነሳሳ መሆኑን አስረድተዋል። ኢትዮጵያን የአፍሪካ ብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ለተያዘው እቅድ የጤናው ዘርፍ ቁልፍ አስቻይ ተብሎ መለየቱን ያነሱት ደግሞ የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝዳንት ታፈሰ ማቲዎስ(ዶ/ር) ናቸው። ዘመናዊ መረጃ ስርዓት ጤናማና አምራች ዜጋ ለማፍራት ወሳኝ መሆኑንና የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሚኒስቴር የተጀመረው የጤና መረጃ ስርዓትን የማጠናከር ተግባር እየደገፈ መሆኑን ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ የጤና መረጃ ስርዓትን ዲጂታላይዝ ለማድረግ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ስድስት ዩኒቨርሲቲዎችና 11 ወረዳዎች እውቅና ተሰጥቷል።
በክልሉ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማሳካት ትምህርት ቤቶችን መሰረት ያደረጉ ሥራዎች ተጀምረዋል
May 11, 2026 159
ባህር ዳር፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማሳካት ትምህርት ቤቶች ላይ መሰረት ያደረጉ ሥራዎች መጀመራቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የተማሪዎችና የትምህርት ቤቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስልጠናና ውድድር አካሂዷል። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ የውድድሩ አስተባባሪ አቶ ሃብታሙ ላቀ እንደገለጹት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ትምህርት ቤቶች ላይ ትኩረት በማድረግ እየተሰራ ነው። ለተግባራዊነቱም ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራን ለማሳደግ ስልጠናዎችና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ፕሮጀክት ውድድር በማድረግ ልምድ የሚቀስሙበትን አውድ ለማስፋት መሰራቱን ጠቁመዋል። የእዚሁ አካል የሆነውና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ፕሮጀክት ተወዳድረው ከ1 እስከ 3 በመውጣት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡት ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት መስጠቱንም አስረድተዋል። ማበረታቻውም ተማሪዎችና ትምህርት ቤቶች በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ላይ አተኩረው በመስራት የዲጂታል ኢትዮጵያ ግቦችን ለማሳካት የላቀ ተነሳሽነት እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል። በቢሮው የኤሌክትሮኒክስ መንግስት አገልግሎት ቡድን መሪና የውድድሩ ዳኛ አቶ ደጀኔ ብርሃኔ በበኩላቸው የተማሪዎችን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ ችግር ፈች ሥራዎችን ለማህበረሰቡ እንዲያቀርቡ መሰራቱን ጠቁመዋል። ለውድድሩ የቀረቡት ፕሮጀክቶችም የዚሁ ሥራ አካል መሆናቸውን ጠቁመው፣ መመዘኛዎቹ የፈጠራ ጽንሰ ሃሳብ ችግር ፈችነት፣ የፈጠራው አተገባበር ጥራት፣ አረዳድና አቀራረብ ላይ መስረት ያደረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ውድድሩ ተማሪዎች በቀጣይ በቴክኖሎጂና በመካኒካል የፈጠራ ሥራዎች የጀመሯቸውን ተግባራት ዳር በማድረስ ለአገር ጥቅም እንዲያውሉና ሌሎች ተማሪዎችም የእነሱን ፈለግ እንዲከተሉ መነሳሳት የፈጠረ ነው ብለዋል። ከካቶሊክ ትምህርት ቤት የመጣው የ10ኛ ክፍል ተማሪ ቅዱስ አላምረው የግብርናውን ዘርፍ ችግር የሚፈታ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤት በማቅረብ 1ኛ በመውጣት ተሸልሟል። የፈጠራ ሥራው ለአርሶ አደሩ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ገልጾ ይህም የመሬት ለምነት፣ የአየር ጸባይን እና የዝናብ ሁኔታን በመለየት ምን አይነት ሰብል መዘራት እንዳለበት መረጃ የሚሰጥ መሆኑን ነው የገለጸው። የጣና ሃይቅ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ አብርሃም ዮሴፍ በበኩሉ በውድድሩ “የቤት ጥበቃ ሲስተም” የፈጠራ ስራ በማቅረብ 2ኛ ደረጃን አግኝቶ መሸለሙን ገልጿል። ፕሮጀክቱም በመኖሪያ ቤት ላይ የሚደርስን በጭስ መታፈን፣ የእሳት አደጋ፣ የስርቆት ወንጀልና ሌሎች አደጋዎችን ለመከላከል የሚያስችል ነው ብሏል። ከዚህ በተጨማሪ የመኖሪያ ቤትን ሙቀት መጥኖ በመቆጣጠር የነዋሪዎችን ጤንነትና ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችል መሆኑን ጠቁሞ ፕሮጀክቱ በቀላሉ የሚተገበርና አዋጭ መሆኑን ገልጿል። ለሦስት ቀናት በተካሄደው የስልጠናና የውድድር መድረክ ከሰባት ትምህርት ቤቶች የመጡ ተማሪዎች 19 የፈጠራ ፕሮጀክቶችን ያቀረቡ ሲሆን በውድድሩ ከ1 እስከ 3 ለወጡትም ቢሮው የገንዘብ ሽልማት አበርክቷል።
ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የግብርና ምርምሮችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመላከተ
May 9, 2026 378
ሐረር፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የአየር ንብረት ለውጥን ታሳቢ ያደረጉ ምርምሮችን ማጠናከር ይገባል ሲሉ ምሁራን አመላከቱ። የአየር ንብረት ለውጥ በግብርና ምርታማነት፣ በሰው ጤና እና በቱሪዝም ዘርፎች ላይ የሚያስከትላቸውን ተግዳሮች በቴክኖሎጂ ታግዞ መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ዓለምአቀፍ ኮንፍረንስ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። በኮንፈረሱ ዘመናዊ ግብርናን ለማስፋፋትና ማኅበረሰባዊ ችግሮችን በፈጠራ ታግዞ ለመፍታት በዳታ ሳይንስ የታገዘ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ ማዋል ወሳኝ መሆኑም ተመላክቷል። በኢትዮዽያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የባዮ ቴክኖሎጂ ምርምር ዳይሬክተር ደጀኔ ግርማ (ዶ/ር) የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን ታሳቢ ባደረገ የግብርና ምርምር ሥራዎች ማስደገፍ ይገባል ብለዋል። በዚህም ኢንስቲትዩቱ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚከሰቱ ተግዳሮቶችን ለመቀነስ የተለያዩ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የምርምር ሥራዎችን ቀርጾ እየሰራ መሆኑን ተናገረዋል። የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ምክትል ፕሬዚዳንት ይስሃቅ ዩስፍ (ዶ/ር) የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትን በቴክኖሎጂ በታገዘ ምርምር በመፍታት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ይገባል ነው ያሉት። ዩኒቨርሲቲው ዲጂታል ቴክኖሊጂንና ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም የተለያዩ የምርምር ፕሮጀክቶችን እያከናወነ መሆኑንም አንስተዋል። ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ተጋላጭ ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ የሰሜኑ ክፍል መሆኑንና ችግሩን አስቀድሞ በምርምር በመፍታት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ተገቢ ነው ያሉት የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) ናቸው። ኮንፍረንሱ የአየር ንብረት ለውጥ በግብርና ምርታማነት፣ በሰው ጤና እና በቱሪዝም ላይ የሚያስከትለውን ተግዳሮት በቴክኖሎጂ ታግዞ መፍታት በሚቻልበት ላይ አተኩሮ መካሄዱን የገለጹት ደግሞ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል ዩሱፍ (ዶ/ር) ናቸው። ተመራማሪዎችና ምሁራን አበርክቷቸውን እንዲያጎለብቱ ምቹ ሁኔታ መፍጠር የሚያስችል እንደሆነም ጠቅሰዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት ታግዞ የሚከናወኑ የምርምር ሥራዎች የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የጤና ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑንም አመልክተዋል ለሁለት ቀናት በተካሄደው ኮንፍረንስ ተመራማሪዎች፣ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ የፌዴራልና የክልል ሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባላትና ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን የምርምር ውጤቶችም ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
ስፖርት
የመውረድ ስጋት ያለበት ቶተንሃም ከሊድስ ዩናይትድ አቻ ተለያየ
May 12, 2026 68
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት ቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ሊድስ ዩናይትድ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማቲስ ቴል በ50ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠረው ጎል ቶተንሃም መሪ ሆኗል። ዶምኒክ ካልቨርት-ሉዊን በ74ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ያሳረፈው ጎል ሊድስ ዩናይትድን አቻ አድርጓል። በሊጉ ያስቆጠረውን ጎል ብዛት ወደ 13 ከፍ አድርጓል። በመጀመሪያው አጋማሽ ቶተንሃም፣ በሁለተኛው የጨዋታው ክፍለ ጊዜ ሊድስ ዩናይትድ የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል። ለረጅም ወራት በጉዳት ምክንያት ከሜዳ ርቆ የነበረው የቶተንሃም አማካይ ተጫዋች ጀምስ ማዲሰን ወደ ሜዳ ተመልሷል። ውጤቱን ተከትሎ ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ38 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። 18ኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው ዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ከፍ አድርጓል። የሰሜን ለንደኑ ክለብ አሁንም የመውረድ ስጋት አለበት። በሊጉ መቆየቱን ያረጋገጠው ሊድስ ዩናይትድ በ44 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ከቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ዌስትሃም ዩናይትድ ማን በሊጉ ይቆያል? ማን ይወርዳል? የሚለው ጉዳይ አጓጊ ሆኗል። ጨዋታውን ተከትሎ 36ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ከግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ቦሌ ክፍለ ከተማ ድል ቀንቶታል
May 11, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቦሌ ክፍለ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ምህረት አየለ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። የግቦቹ ባለቤት ምህረት አየለ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። በሊጉ 12ኛ ድሉን ያስመዘገበው ቦሌ ክፍለ ከተማ በ43 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ከሁለት ተከታታይ ድሎች በኋላ የተሸነፈው ሸገር ከተማ በ47 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ረግቷል። በውድድር ዓመቱ በአጠቃላይ ስድስተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ የ26ኛ ሳምንት ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ እና መቻል ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
ነገሌ አርሲ ወሳኝ ድል ተቀዳጅቷል
May 11, 2026 145
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ነገሌ አርሲ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 0 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዳዊት መለሰ እና ከቤ ብዙነህ በጨዋታ፣ ዳዊት ተፈራ በፍጹም ቅጣት ምት ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ነገሌ አርሲ በ51 ነጥብ ደረጃውን ከሶስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ዝቅ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ 13ኛ ድሉንም አስመዝግቧል። በአንጻሩ በሊጉ 11ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ34 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት አምስት ጨዋታዎች አላሸነፈም። ዛሬ በተደረገ ሌላኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 1 አሸንፏል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 31ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ32ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ከግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ መድን በድል ጉዞው ቀጥሏል
May 11, 2026 116
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዳዊት አውላቸው በጨዋታ እና ረመዳን የሱፍ ግቦቹን አስቆጥረዋል። የኢትዮጵያ መድኑ አብዱ መሐመድ በራሱ መረብ ላይ ያስቆጠራት ጎል ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቸኛ ግብ ሆና ተመዝግባለች። በሊጉ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮጵያ መድን በ40 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 10ኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉም ዘጠነኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 11ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ38 ነጥብ ከነበረበት 12ኛ ደረጃ ወደ 13ኛ ዝቅ ብሏል።
አካባቢ ጥበቃ
የአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
May 11, 2026 230
አዲስ አበባ፤ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፡-73ኛው የታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም (GHACOF 73) ግንቦት 10 እና 11 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል። ፎረሙ የሚካሄደው “የአየር ንብረት አገልግሎቶች፤ ለአይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና የመተግበሪያ ማዕከል(ICPAC) ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን ፎረሙን እንዳዘጋጀው ተገልጿል። ስብሰባው ትንበያ ከመስጠት ባለፈ ትንበያዎቹን ወደ ተግባር መቀየር እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የቅድመ ማስጠንቀቂያና ቅድመ ዝግጅት እርምጃዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። የአየር ንብረት መረጃዎች አርሶ አደሮች ፣ የጤና ባለሙያዎችን እና የአደጋ ስጋት አመራሮችን በቀጥታ እንዲደግፉ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። በብሔራዊ የሚቲዎሮሎጂ ተቋማት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር ሌላኛው የመወያያ አጀንዳ ነው። መድረኩ ለታላቁ የአፍሪካ ቀንድ ግብርና እና የውሃ ሀብት ወሳኝ የሆነውን ከእ.አ.አ ከጁን እስከ ሴፕቴምበር 2026 ያለውን የዝናብ ወቅት ትንበያ ይቀርብበታል። ሚኒስትሮች፣ የምርምር ተቋማት፣ ሰብአዊ ድርጅቶች፣ የሲቪክ ማህበራት እና የግል ባለሀብቶች ይሳተፋሉ።ይህ የተሳታፊዎች ስብጥር ሳይንስን ከፖሊሲ ጋር ለማገናኘት የታለመ ነው። የአየር ንብረት መዛባት የሩቅ ስጋት መሆኑ ቀርቶ በደጃፋችን ላይ ያለ ተጨባጭ አደጋ ነው ያለው ኢጋድ ፎረሙ በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የሚገኙ ማህበረሰቦች በቂ መረጃ እንዲኖራቸውና አስቀድመው ዝግጁ እንዲሆኑ ማስቻል ላይ ትኩረቱን ያደረገ መሆኑን አመልክቷል።
የኢትዮጵያ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ ስኬታማ የልማት መርሃ ግብሮች የበለፀገ የደን ሃብት እንዲፈጠር እያደረገ ነው
May 9, 2026 334
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ ስኬታማ የልማት መርሃ ግብሮች የበለፀገ የደን ሃብት እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በተያዘው በጀት ዓመት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት መርሃ ግብር 3 ነጥብ 9 ሚሊየን ሄክታር መሬት መልማቱንም አስታውቋል። በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈፃሚ ፋኖሴ መኮንን፤ የሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋ የፈጠረው የደን መመናመን ከፍተኛ የአካባቢ መራቆትን አስከትሎ ነበር ብለዋል። ይህም የኢትዮጵያ የአፈር ለምነትን በመቀነስ በግብርና ምርታማነት፣ በዱር እንስሳትና ዕፅዋት ደኅንነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል። በዚህም በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ማግስት በአረንጓዴ አሻራና የአካባቢ ጥበቃ ልማት መርሃ ግብር የሥነ-ምኅዳር ደኅንነት እንዲያገግም ያስቻለ ስኬታማ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በተለይም በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ የህብረተሰቡን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትን ባህል በማጎልበት የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን እያስጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመትም በ22ሺህ 59 ተፋሰሶች 4 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለማልማት በተያዘው ዕቅድ፤ እስካሁን 3 ነጥብ 9 ሚሊየን ሄክታር መሬት በበጋ ተፋሰስ መልማቱን አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅትም በተለያዩ ክልሎች የሥነ-ምኅዳር ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ የልማት ሥራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት ዓመታት በህብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ሰፋፊ የአፈርና ውሃ ጥበቃ የልማት ሥራዎችም የተራቆተ የመሬት ገፅታ እንዲያገግም በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን አስረድተዋል። የህብረተሰቡ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ባህል እያደገ መምጣቱም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም በርካታ ዜጎች በንብ ማነብ፣ እንስሳት መኖ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት መርሃ ግብሮች ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። ይህም የህብረተሰቡን የአካባቢ ጥበቃ ባለቤትነትን በማረጋገጥ ኢትዮጵያ በደን ሀብት የበለጸገች ለምለም ሀገር እንድትሆን እያደረጋት መሆኑን አንስተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል
May 9, 2026 251
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡ ተገለጸ። በቢሮው የደን ልማት እንክብካቤ ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን ስዩም ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክረምቱ ወቅት ለሚከሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር የደን ሽፋንን በመጨመር፣ የደረቁ ምንጮች እንዲያገግሙ በማድረግ እና የግጦሽ መሬት መጠንን በመጨመር አመርቂ ውጤት ተመዝግቦበታል ነው ያሉት፡፡ በአሁኑ ወቅትም በክልሉ 71 ተራሮችን የማልማት ስራ እየተከናወነ ሲሆን ቡለውጡ አመታት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት 18 ነጥብ 9 ከመቶ የነበረውን የደን ሽፋን ከ 23 ነጥብ 8 በመቶ በላይ ማድረስ መቻሉንም ተናግረዋል። ይህንን ለማስቀጠልም በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 180 ሺህ ሔክታር መሬት በተለያዩ ችግኞች ለመሸፈን እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት ። ለዚህም የችግኝ፣ የጉድጓድ እና ሌሎች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች በበቂ ሁኔታ መደረጉን አመልከተው በአሁኑ ወቅትም የበልግ ወቅት የችግኝ ተከላ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። የችግኝ ተከላው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ትልቅ አበርክቶ እንዳለው አመልክተው ለክረምት ወቅት ተከላ የሚደረገው ዝግጅት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በዘርፉ የተመዘገበውን ለውጥ ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ሊረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዞኑ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል
May 8, 2026 346
ጊምቢ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ በምእራብ ወለጋ ዞን ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታቸው የጎላ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ እንዳሉት በዞኑ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል። ከችግኞቹም መካከል ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታቸው የጎሉ የቡና፣ የአቮካዶ፣ የማንጎ፣ የፓፓያ እና ሌሎች እንደሚገኙበት አስረድተዋል። የችግኝ ተከላው በበጋ ወራት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ፣ ለእንስሳት መኖ እንዲውልና ለም አፈር በጎርፍ እንዳይወሰድ ለመከላከል ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱ ተገልጿል። ይህም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ችግኞቹን በበጋ ወራት በተከናወኑ የተለያዩ የእርከን ስፍራዎችና የተመረጡ ቦታዎች ለመትከልም እስካሁን ከ117 ሚሊዮን በላይ ጉድ ጓዶች ቁፋሮ መከናወኑን አቶ ፍቅሩ ጠቅሰዋል። ስራውን ለማሳካትም አርሶ አደሩን በማሳተፍ መከናወኑን የጠቀሱት ሀላፊው፤ የግብርና ባለሙያች ድጋፍና ክትትል ስራዎች መጠናከራችውን አንስተዋል። ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውን የጠቀሱት ደግሞ የጊምቢ ወረዳ አርሶ አደር ዋኬኔ አምሳሉ ናቸው። ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞችን ጽድቀት መጠን ለማሳደግ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በመንከባከብ ከሰውና እንስሳት ንክኪ መጠበቃቸውን ተናግረዋል። ዘንድሮም በመንግስት ከሚለሙት ችግኞች ባለፈ እሳቸው በግላቸው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞችን ማፍላታቸውን ጠቁመዋል። ከዚህ በፊት ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት ባለመስጠታቸው ያጡትን ምርታማነት በሚያካክስ መልኩ በመጪዉ ክረምት የሚተከሉ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች በብዛት ማዘጋጀታቸው የገለጹት የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ለሊሳ ኤቢሳ ናቸው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በተሰራው ስራ በርካታ ጥቅም በማግኘታቸውም ስራውን ለማስቀጠል ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት ይገባል
Apr 28, 2026 1314
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት እንደሚገባ የሕብረቱ ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃጸም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 ጎን ለጎን የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው። የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድን ሀገር በቀል በማድረግ አካታች ዕድገትና ዘላቂ የኢኮኖሚ ሽግግርን የሚያፋጥን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ገልጸዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራትም ብሔራዊ የልማት ዕቅዶችን ከአጀንዳው ጋር በማጣጣም የበጀት ድልድልና የፖሊሲ እርምጃዎችን ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካ አጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦች የበለጸገች አህጉርን እውን ለማድረግም የአባል ሀገራት ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። የአጀንዳ 2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን በማሳካት የተሳለጠ የለውጥ ሽግግርን ለመፍጠርም ጠንካራና የተሰናሰለ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና አህጉራዊ የፖሊሲ ፍሰት ሊኖር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ለዚህም የመንግሥታት፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች በወሳኝ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ የሚኖራቸውን ትብብርና ቅንጅት የሚያበረታታ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የዑጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትርና ተሰናባቿ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ ቢሮ ሊቀ-መንበር ሮቢናህ ናባንጃ በበኩላቸው፤ የአፍሪካውያን ድምፅ በወሳኝ የዓለም መድረኮች ላይ መንፀባረቅ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ መድረኮች በከፍተኛ ደረጃ ከሚደረግ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ባለፈ በወሳኝ ስትራቴጂክ ሂደቶች ላይ በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ብለዋል። የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካትም ሎጂስቲክስ፣ ትራንስፖርትና መሰል የትኩረት ዘርፎች ላይ በስፋት በመሰማራት ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች ነው
Apr 28, 2026 802
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃፀም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 በትይዩ የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው። በአፍሪካ አካታች ዕድገትና ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ሽግግር ለመፍጠር ወሳኝ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድ ሀገር በቀል እንዲሆን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ተናግረዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራት ብሔራዊ የልማት ዕቅዶቻቸው ከአጀንዳው ጋር እየተጣጣመ መምጣቱን በማንሳት፤ የበጀት ድልድልና ፖሊሲዎቻቸው ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ የሰጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን በማሳካት የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ በሀገራት መካከል ያለው ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባም አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸውን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ አለባቸው
Apr 27, 2026 725
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸው ላይ እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከታንዛኒያ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የአፍሪካ ወሳኝ ማዕድናትን ለአረንጓዴ የኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ማዋል" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጁት የ12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ቅድመ ጉባኤ ተካሂዷል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ እንደ ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ግራናይት እና ሌሎች የከርሰ ምድር ሀብቶችን ጨምሮ የዓለምን 30 በመቶ ማዕድናትን ይዛለች፡፡ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻዋን የዓለምን ከፍተኛ የኮባልት ማዕድን የያዘች መሆኑን ገልጸው፤ ይሄውም አፍሪካን የዓለም አቀፍ የኃይል ሽግግር /Energy Transition/ ማዕከል ያደርጋታል ብለዋል፡፡ አፍሪካ ዩራኒዬምና ሌሎች የከርሰ ምድር የከበሩ ማዕድናት ባለቤት መሆኗን በመጥቀስ፤ ለዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል አቅርቦት አስተዋጽኦ ከማድረግ ባለፈ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ኒውክሌር ኃይል ልማት እያመሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አፍሪካ የከበሩ ማዕድናት ባለቤት ብትሆንም አብዛኛው በጥሬ እቃ መልክ ወደ ውጭ የሚላክ በመሆኑ የአህጉሪቱ የእርስ በእርስ ግብይት ከሁለት በመቶ እንዳማይዘል ተናግረዋል፡፡ በአህጉሪቱ የማዕድናት ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን መገንባት ቢቻል በየዓመቱ ከ24 ቢሊየን ዶላር በላይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘትና ለ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ይቻላል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ የማዕድን ፖሊሲ ለእሴት መጨመር፣ ኢንዱስትሪ ልማትና ሁሉን አቀፍ ልማት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአህጉሪቱ የተቀናጀ ቀጣናዊ ኢንዱስትሪ ለመገንባት ያለውን ፍላጎት በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አህጉራዊ የማዕድን ሀብቶችን ወደ ዘላቂ ብልጽግና መለወጥ ይገባል ብለዋል፡፡ በዚህም የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቀጣናዊ እሴት ሰንሰለትን በማጠናከር የማዕድን ጸጋዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚደረገው ጥረት ትብብሩን ማጠናከሩን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካዳሪ ሲንጎ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍና አካታች ዕድገት ለማስመዝገብ የማዕድን ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በተፈጥሮ ሀብታችን ላይ የሚኖረን ትብብርና ተሳትፎ ስትራቴጂያዊና መዳረሻ ግብ ያለው መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮት ሽግግርን ለመፈጠር በአቅም ግንባታ ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 1111
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 278
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 508
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች
May 3, 2026 591
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር እያሸጋገራት ይገኛል።የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የመሰረተ ልማት እና የተቋማት ግንባታ ስራዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋንኛ ስራዎች ናቸው። ለውጡን ተከትሎ መንግስት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን ስትራቴጂ በመቅረጽ የዲጂታላይዜሽን ስራውን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶ አድርጎታል። የለውጡ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ ቴክኖሎጂን እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመቁጠር "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን አጠቃላይ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ተግባር ገባ።ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱን የዲጂታል ጉዞ ከመሰረቱ የለወጠ ሲሆን፣የመጀመሪያው ትልቅ እርምጃም የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ነበር። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ የኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል።በተለይም የአምስተኛ ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን አስችሏታል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ለውጡ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ውጤት አምጥቷል።እንደ ቴሌብር (telebirr) ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ምንም የባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ፣ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር ትልቅ መደላድል ፈጥረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ አድማስ ይበልጥ አስፍተውታል። የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ራዕይ ለዓለም ያሳየችበት አጋጣሚ ነው።ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የካንሰር ህመምንና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ መለየት የሚያስችሉ የኤአይ ውጤቶችን አበልጽጓል። በግብርናውም ረገድ የአፈርን ለምነትና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ዋስትና ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል ዓለም ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የፋይዳ (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን መረጃ በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የለውጡ ፍሬያማነት ማሳያ ነው።የሳይንስ ሙዚየምም የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያሳይና የሀገሪቱን ቴክኖሎጂ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ሆኗል።የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቅርቡ መጠናቀቁ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2025 ስትራቴጂው መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዲጂታል 2030ን ይፋ ሲያደርጉ የነበረው ትልቁ መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች የሚል ነው። ስትራቴጂው በዋናነት"የፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት፣ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠር፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) አድርጎ መገንባትን እንደ ዋነኛ ግብ አስቀምጧል። ይህም ሁሉን አቀፍ የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ የመንግስት አገልግሎቶችን መቶ በመቶ ወረቀት አልባ በማድረግ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) በግብርና፣ በጤናና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ በስፋት በመተግበር የምርታማነት አብዮት መፍጠርን ያለመ ነው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ስራ በአህጉራዊ ደረጃ ያለውን ተቀባይነትና የተሰጣትን ትልቅ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት የቴክኖሎጂ ከፍታ፣ ሀገሪቱን በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ተፎካካሪ ብቻ ሳይሆን የፈጠራ ምንጭ እንድትሆንም እያደረጋት ይገኛል። በዚህ ረገድም የቀጣዩ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ስኬትም ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና በቴክኖሎጂ የበለጸገች ሀገር የማድረግ ራዕይን ለማሳካት እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ ያገለግላል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 3, 2026 458
ክልሎች፤ሚያዝያ 25/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮች በወፍ በረር ሲቃኙ ይህንን ይመስላሉ!!! 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡትን የቶዮ ሶላር ኢነርጂ ምዕራፍ ሁለት፣ የኦሪጂን እና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካን በይፋ መርቀዋል። እነዚህ የሶላር ፋብሪካዎች በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን፣ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅን እና 7 ቶን ሃይድሮጅን ለገበያ ያቀርባል። ይህ ክንውን የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ለማፋጠን፣ የኢነርጂ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ዘላቂ፣ የማይበገር ሁለንተናዊ እድገት ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል። 👉እንቁላልን ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት የማቆየት ልምምድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ፤ የዶሮ እንቁላል ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት ያህል ማቆየት የሚያስችል ቴክኖሎጂን ወደ ተግባር ለማስገባት ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል። በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ሕክምናና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ማስተዋል ብርሃን፤ ዩኒቨርሲቲው የእንቁላል ምርት ብክነትና ብልሽትን ለማስቀረት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። በዚህም እንቁላልን እስከ ሁለት ዓመት ያለ ምንም ብልሽት ማቆየት የሚያስችለውን ቴክኖሎጂን የማላመድና የማስተዋወቅ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂው በአንድ ሊትር ውሃ ውስጥ 30 ግራም የኖራ አፈር ወይም ላይም ስቶን ጨምሮ በማዋሃድ እስከ 12 እንቁላሎችን ሳይበላሽ የሚያስቀምጥ በመሆኑ ለአርሶ አደሩ ተመራጭ ነው ያሉት። ይህም እስካሁን ባለው አንድ ትኩስ እንቁላል ሳይበላሽ መቆየት የሚችለው እስከ ሁለት ሳምንት መሆኑን ጠቁመው ቴክኖሎጂው ይሄን ችግር በመሰረታዊነት የሚቀይር ነው።፡ ቴክኖሎጂውን በስፋት በማስተዋወቅና በማላመድ ረገድም ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን በመስጠት ችግር ፈቺነቱን የማሳየት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። 👉የአፋር ጥጥ ተስፋ ሰጪ ፀጋ! የአፋር ክልል የበርካታ የተፈጥሮ ፀጋዎች ባለቤት ነው፤ ሆኖም እነዚህን እምቅ ሀብቶች ወደ ልማት በመቀየር ከፀጋዎቹ ተቋዳሽ ለመሆን ሳይቻል ለረጅም ተቆይቷል። አሁን ግን ከፀጋዎቹ አንዱ የሆነውን ተፈጥሯዊ ጥጥ (Organic Cotton) ለማምረት ተስፋ ሰጪ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በሰመራ በተካሄደ የውይይት መድረክም በግብርና ሚኒስቴር የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳምሶን አሰፋ፤ የአፋር ክልል ጥጥን በመስኖ ማልማት የሚቻልበት አቅም ያለው በመሆኑ ልማቱን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሀገራችን የጥጥ ልማትን ለማስፋፋት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው፤ ባለፈው የምርት ዘመን እንደ ሀገር በስድስት ክልሎች 110 ሺህ ሄክታር መሬት በጥጥ መልማቱን ተናግረዋል።በዚህም 79 ሺህ ሜትሮክ ቶን የተዳመጠ ጥጥ በማምረት ለኢንደስትሪዎች ማቅረብ እንደተቻለ ነው የገለፁት። 👉የሸማቹ ሸክም ይቀላል! የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ስድስት ከተሞች ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ ሲያካሄድ የህብረት ስራ ማህበራት ከእንግዲህ የሸማቹን ሸክም ሊያቀሉ ይገባል የሚል ሀሳብ ተነስቷል። በሀዋሳው በተካሔደው የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለያዩ መስኮች የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊት ሀገር ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን አንስተዋል። በተከናወኑ ተግባራትም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አክለዋል። የመንግስትን፣ የግሉ ዘርፍንና የዜጎችን የካፒታል አቅምና ዕውቀትን ደምረው የያዙት የህብረት ስራ ማህበራት ግብርናውን በማሻገር የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት በመቀየር ረገድ ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልፀው የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመፍታትና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር የሸማቹን ህብረተሰብ ሸክም ያቀላሉ ተብሎ እንደሚታመንም አስረድተዋል። 👉ምርምር ለቀጣናዊ ትስስር በጅማ ዩኒቨርሲቲ "ቀጠናዊ ሰላምና ትብብር ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ባለችበት ቀጣና የሚታዩ ፍላጎቶችን ለማሟላትና ተግዳሮቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመፍታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ተነስቷል። በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጦሽኔ ቀጣናውን በልማት ለማስተሳሰር በሚደረግ ጥረት የትምህርት ተቋማቱ የጥናትና ምርምር ድጋፍ ከፍተኛ ሚና አለው ያሉ ሲሆን ለዚህም ተቋማቱ ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያሳድጉ እና ማህበራዊ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚያግዙ የፖሊሲ መነሻ ሀሳቦችን በጥናትና ምርምር እንዲያፈልቁ አሳስበዋል። የሚወጡ ጥናቶች በቀጣናው በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ እየተከሰቱ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሊሆኑ እንደሚገባ የተጠቀሰ ሲሆን ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን በመተግበር እያከናወነች ያለችው ተግባር በተመክሮነት ቀርቦ አድናቆትን አስገኝቶላታል። 👉ሻይ ቅጠል አሁን አሁን አርሶ አደሩ በተለያዩ ኢንሼቲቮች በሚከናወኑ የግብርና ልማት ትግበራዎች ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። በርካታ አርሶ አደሮች በሻይ ቅጠል ልማት ኢንሼቲቭ በመሰማራት ገቢን ከማሳደግ ባለፈ ለሌሎችም ሰፊ የስራ ዕድል እየፈጠሩ ይገኛሉ። በጅማ ዞን የሻይ ቅጠል ልማትን ከማስፋፋት ባለፈ የበያ ትስስር የመፍጠርና ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለፋብሪካ ለማቅረብ ለአርሶ አደሩ ግንዛቤ እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም፤ በዞኑ የሻይ ቅጠል ልማትን በኢኒሼቲቨን መልክ በመተግበር የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድል እየተፈጠረ ነው። ዘንድሮም ስራውን ለማስቀጠል በተመረጡ 6 ወረዳዎች በመጪው ክረምት የሚተከሉ 50 ሚሊዮን ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን ህዝብን በማሳተፍም ወደ 2 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬትን ለመሸፈንም ታስቧል። ጥቅሙ የገባቸው አርሶ አደሮችም የሰብል ልማቱን ለጊዜው ተወት በማድረግ በሻይ ቅጠል ልማት ላይ እየተሳተፉ እንደሆነ ይናገራሉ። በዞኑ የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አርሶ አደር ሲራጅ ሼክ ከድር በሻይ ቅጠል ልማት ላይ መሳተፍ ከጀመሩ ወዲህ ገቢያቸው መጨመሩን ተናግረዋል። አርሶ አደር ሱልጣን አባሞጋ በበኩላቸው ተሰማርተውበት ከነበረው የሰብል ልማት ወደ ሻይ ቅጠል ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአካባቢ ፀጋን ተገንዝቦ ወደ ስራ መግባት ተጠቃሚነትን እንደሚያመጣ ማሳያ ሊሆን ይችላል። 👉ተስፋዎች ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በሆሳዕና ከተማ የተካሄደው የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ደረጃ ሽግግር እውቅና መርሃ ግብር ይጠቀሳል። "የኢንተርፕራይዞች ሽግግር ለእመርታዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ የተከናወነው የዕውቅና መድረክ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት ነው የተካሄደው። እሳቸው እንደገለፁት፤ ኢንተርፕራይዞቹ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ ነው። በክልሉ በገጠርና በከተማ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ ከ25 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ መስኮች መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በጥቃቅንና በአነስተኛ ደረጃ የሚገኙ 4 ሺህ 948 ኢንተርፕራይዞችን የማሸጋገርና 495 ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን የመለየት ስራ መሰራቱም እንዲሁ። ከኢንተርፕራይዝ ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሸጋገሩ አምራቾች እንደተናገሩት ሽግግሩ ስራቸውን በተሻለ ሁኔታ ለመከወን እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል። 👉ትምህርትና አርብቶ አደሩ የወፍ በረር ቅኝታችንን ስንቀጥል ጋምቤላ እንደርሳለን፤ በሳምንቱ በጋምቤላ ከተማ በተካሄደ መድረክም የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውም ተመልክቷል። በለውጡ ዓመታት የአርብቶ አደሩን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ውጤት መመዝገባቸውም እንዲሁ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም ረገድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና የገዘፈ መሆኑም በመድረኩ መገለፁን ቅኝታችን ዳሶታል። 👉ልወቅሽ ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ጠቅለል አድርጎ የዳሰሰው ቅኝታችን ደግሞ በስድስት ከተሞች ለማካሄድ ዕቅድ የተያዘለትና እስካሁን በጅማ፣ በሀዋሳና በደብረ ብርሃን ከተሞች የተካሄደው የ"ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ታላቁ ሩጫ" ከተሞቹን ከማስተዋወቅ የዘለለ ፋይዳውን በመርሃ ግብሩ ላይ በተላለፉ መልዕክቶቹ አሳይቷል። ለአብነት በጅማ የተካሄደው ‘ፖሊዮን በጋራ እናጥፋ’ የሚለውን የጤና ጉዳይን ያነሳ ነበር። በአዳማ ከተማ የተከናወነው ሁነት ደግሞ በመኪና ውድድር ታጅቦ የተከናወነና የቱሪዝም መስህቦችን ማስተዋወቅን ታላሚ ያደረገ ነበር። ‘’ለሀዋሳ ከፍታ እንሮጣለን’’ በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ሁነትም ከጅማና አዳማው ሁነት የተለየ እሳቤንም ሆነ መልዕክትን አልያዘም። ሁሉም ሁነቶች ከዋነኞቹ አምስት ምጣኔ ሃብታዊ አምዶች መካከል አንዱ የሆነውን ቱሪዝም ልማት በማጠናከር የማህበረሰቡን የዘርፉ ተጠቃሚነት ማላቅን ታሳቢ ማድረጋቸውን መመልከት ተችሏል። ቅኝቶቻችን በወፍ በረር ይህንን ይመስላሉ!! የሳምንት ሰው ይበለን!!!
ትንታኔዎች
ለተቃና ነገ የኢትዮጵያ ትጋት አንዱ መገለጫ
May 11, 2026 402
(በዮሐንስ ደርበው) ኢትዮጵያ ከምትከውናቸው ዐበይት ጉዳዮች መካከል ሰው ተኮር ተግባራት ቀዳሚው ነው። በአዲስ አበባ በተካሄደው ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ጥረት ሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ ነው ብለዋል። መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል አድርጎ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በዚህም መሠረት፤ የልጆች ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት፣ የምገባ ሥርዓትን ማሳደግ፣ የሕጻናት መጫወቻ ሥፍራዎች ግንባታ ላይ ተጨባጭ ውጤቶች መምጣታቸውንም ነበር የጠቀሱት። ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማትና ትምህርት ፖሊሲ የዘላቂ ብልጽግና መንገዳችን ከሆነው የመደመር ዕሳቤ ጋር በተናበበ መልኩ እየተተገበረ በስኬት ቀጥሏልም ብለዋል። ኢትዮጵያ ለነገ የተዘጋጀ ትውልድ ለመገንባት በሕግና በፖሊሲ የተደገፉ የቀዳማይ ልጅነት ኢኒሼቲቮችን እየተገበረች እንደምትገኝም አስታውቀዋል። ለአብነትም፤ በ2015 ተሻሽሎ የፀደቀው ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማት እና ትምህርት የፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲሁም በ2017 የፀደቀውን አጠቃላይ የትምህርት አዋጅ መሠረት በማድረግ ከ35ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላው ሀገሪቱ እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል። በመንግሥት ተቋማት የሕጻናት ማቆያ ማዕከላት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በመጠቆምም፤ ኢትዮጵያ የሕጻናትን ደኅንነት ማሻሻል የሚያስችል ጉልኅ ብሔራዊ መርሐ-ግብር መጀመሯን አንስተዋል። በሰቆጣ ቃል ኪዳን አማካኝነት የ15 ዓመት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ ከሁለት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ላይ የሚደርሰውን መቀንጨር በ2022ዓ.ም ዜሮ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። የሌማት ትሩፋትና የአልሚ ምግቦች ምርታማነት የሕጻናትን ጉዳት ለመቀነስና የልጆችን ጤናማነት መጨመር እያስቻሉ እንደሚገኙም ነው የተናገሩት። ኢትዮጵያ ለዘላቂ የልማት ግቦችና ለሕጻናት መብቶች ጥበቃ የገባቻቸውን ቃል ኪዳኖች ወደ ተግባር እየለወጠች መሆኑን በማንሳት፤ ይህንንም አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። መንግሥት ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን በመላ ሀገሪቱ ለማስፋት ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑንም አመላክተዋል። በዚህም መሠረት፤ በጀት በመመደብ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል፣ የተማሪዎችን ምገባ በማስፋፋት ውጤት ማምጣቱን ነው የሚያብራሩት። ልጆች በአካልና በመንፈስ የሚጎለብቱባቸው የስፖርትና የመዝናኛ ቦታዎች በየአካባቢው በመገንባት፣ በኮሪደር ልማት ለልጆች ምቹ ሥፍራ እየተፈጠረ መሆኑንም በመጥቀስ። ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር፣ አኅጉር እና ዓለም ላይ መሥራት በመሆኑ በትጋት ማስቀጠል እንደሚገባም በአጽንኦት ይናገራሉ። አፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ተግዳሮቶችን ለመፍታት የራሷን መፍትሔዎች በማፍለቅ፣ በብሔራዊ የልማት አጀንዳዋ እያካተተች መሆኑን የሚገልጹት ደግሞ የአፍሪካ ቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ከበደ ወርቁ ናቸው። በሕጻናት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ማንኛውም ሀገር በመጪው ትውልድ ላይ ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው እጅግ አስፈላጊ ኢንቨስትመንቶች አንዱ መሆኑንም ያነሳሉ። አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ ያሉባትን ተግዳሮቶች ከመጋፈጥ ባለፈ፤ የራሷን መፍትሔዎች እያመነጨች መሆኑንና ጉዳዩን የብሔራዊ ልማት አጀንዳዋ አካል እያደረገችው እንደምትገኝም ገልጸዋል። አዲስ አበባ ይህን ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ እንድታስተናግድ የተመረጠችበት ዋና ምክንያትም፤ በዘርፉ እያከናወነች ያለው ተግባር አርዓያነት ያለው በመሆኑ ነው ብለዋል። ከተማዋ የጤና እና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎቶችን ያካተተ የተቀናጀ ዘርፈ-ብዙ አሠራር መዘርጋቷን ጠቅሰው፤ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት እና የቀን የሕጻናት እንክብካቤ ማዕከላትን በከተማ አቀፍ ስትራቴጂ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝም ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው፤ መዲናዋ በቀዳማይ ልጅነት ያመጣችው ተጨባጭ ውጤት በአርዓያነት እንድትጠቀስ እንዳደረጋት አንስተዋል። በሕጻናት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች፤ በትምህርት፣ በሰው ሃብት ልማትና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ፋይዳ እንዳለውም አስረድተዋል። በዚህም በአዲስ አበባ ፍትሐዊና አካታች የቀዳማይ ልጅነት ልማት መርሐ-ግብርን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ የትውልድ ግንባታ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል። "ሕጻናት የአዲስ አበባ የነገ ተስፋዎች" የሚል ፍኖተ ካርታ በመቅረጽ 1 ነጥብ 3 ሚሊየን ለሚሆኑ ከስድስት ዓመት በታች ሕጻናት ሁለንተናዊ ዕድገት መረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በትምህርት ቤት ምገባ መርሐ-ግብርም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ ዩኒፎርምና በቀን ሁለት ጊዜ ምግብ በማቅረብ በሕጻናት ክብካቤ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል ነው ያሉት። የሕጻናት ማቆያና መጫወቻ የመሠረተ-ልማት ግንባታ፤ ሕጻናት ነፃ የሕክምና፣ የምገባና የሥነ-ልቦና አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። የቀዳማይ ልጅነት መርሐ-ግብር በ2015 ዓ.ም ሲጀመር በዕድገት ወደ ኋላ የቀሩ የሕጻናት መጠን ከነበሩበት 13 በመቶ አሁን ላይ ወደ 10 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉን ከንቲባዋ አመላክተዋል። አክለውም፤ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዝግጁነታቸው ከነበረበት 49 በመቶ አሁን ወደ 90 በመቶ ማደጉንም ተናግረዋል። ሀገር በሁሉም ዘርፍ የበቃ መጪ ትውልድ እንዲኖራት መንግስት የያዘው ጥረት በሚፈለገው መጠን ለውጤት እንዲበቃ የሁሉንም ትኩረትና ተሳትፎ ይሻል። ለነገ በሁሉም ዘርፍ የዳበረ ትውልድና የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን ዛሬ ላይ እየተደረገ ያለው ርብርብ የሀገራችንን መፃኢ ብሩህ ተስፋ ይበልጥ የሚያለመልም ነውና ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
ትኩረት የተሰጠው የሕጻናት ስነምግብ
May 10, 2026 315
በሙሴ መለሰ በዓለም ላይ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ህጻናት ሙሉ አካላዊ እና አዕምሯዊ አቅማቸውን ላይ ሳይደርሱ እድሜያቸውን ይቆጥራሉ። የዚህ ልብ ሰባሪ ክስተት መነሻ መቀንጨር (stunting) ይባላል። የስነ ምግብ ባለሙያዎች መቀንጨርን በዓለም አቀፍ ደረጃ ስር የሰደደ ቀውስ ያስከተለ እና የጉዳቱ መጠን የገዘፈ ነገር ግን የአስከፊነቱን ያህል በቂ ትኩረት ያላገኘ ጉዳይ ነው ይሉታል። ብዙ እንደ ግጭቶች እና ሌሎች የዓለም ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ቀውሶች አርዕስተ ዜና ሲሆን አይታይም። በቀላሉም የህዝብን ትኩረት አይስብም። ይሁንና የመቀንጨር ጉዳቶች ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ መዘዞች እና የአንድ ሀገር ልማትና ጉዞ ላይ ሊቀለበስ የማይችል ጣጣን ያስከትላል። የህጻናትን ሰውነት ቀስ በቀስ እየጎዳ አዕምሯቸው እና የመፍጠር አቅማቸውን እያደከመ በመሄድ፣ በድምጽ አልባነቱ ውስጥ ውስጡን ዘላቂ መዘዝ እያመጣ ይገኛል። መቀንጨር ህጻናትን በለጋ እድሜያቸው ጊዜ ብቻ ጎድቶ የሚያበቃ ቢሆን መልካም ነበር ዳፋው እስከ ህይወታቸው መጨረሻ የሚከተላቸው ነው። ህጻናት እጅግ በጣም ቁልፍ በሚባለው የእድሜ ክልል ማለትም ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት ባለው ጊዜ ተመጣጣኝ ምግብ ማግኘት ሲገባቸው በምግብ እጦት ምክንያት እድገታቸው አሉታዊ ተጽእኖ ይደርስባቸዋል። የመቀንጨር ጉዳት አካላዊ ብቻ ጉዳት አድርጎ ማየት የችግሩን ሙሉ ምስል እንደማያሳይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ይገልጻል። የመቀንጨር ችግር ያለባቸው ህጻናት ትምህርታቸውን በሚገባ መከታተል እንደማይችሉና በሽታ ተጋላጭነታቸው የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ከሚያገኙ ህጻናት ጋር ሲነጻጻር እጅጉን ሰፊ እንደሆነ አመልክቷል። የአዕምሮ እድገት ውስንነት በማምጣት አቅማቸውን በሚገባ አውጥተው እንዳይጠቀሙ ያደርጋል። ህጻናት በምግብ እጦት መቀንጨራቸውን ዩኒሴፍ የህጻናት መብቶች ጥሰት ሲል ይገልጸዋል። ይህም ትውልድ ለአንድ ሀገር የሚኖረው ድርሻ እንዲኮስስ ያደርጋል። መቀንጨር ድምጽ የለውም ኢኮኖሚን በአንድ ጊዜ አያቃውስም ወይንም ህዝብ ላይ ቶሎ ስጋትን አይጭርም ግን ጉዳቱ አያሌ ነው። በዓለም ላይ ከአምስት ዓመት በታች ከሚገኙ ህጻናት መካከል 23 ነጥብ 2 በመቶው የመቀንጨር ሰለባ መሆናቸውን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያመለክታል። ይህ ችግር የህጻናትን አካላዊና አዕምሯዊ አቅም ከመንጠቅ ባለፈ፣ የሀገርን የረጅም ጊዜ እድገት ወደ ኋላ የሚጎትት መዋቅራዊ ሳንካ ሆኖ ቀጥሏል። በኢትዮጵያ መቀንጨርን ማጥፋት ከምግብ እና ጤና ግቦች በዘለለ ሀገር እንድትበለጽግና እንድታድግ ከሚደረገው ብሄራዊ ውጥን ጋር የተቆራኘ የህልውና ጉዳይ ነው። የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ እድገት መሳካት የጀርባ አጥንት ለሆነው አምራች እና ተመራማሪ ሀይል ግንባታ ያለው አስተዋጽዖ ከፍ ያለ መሆኑ ይታመናል። ምንም እንኳ በሀገራችን የመቀንጨር ምጣኔ እ.አ.አ በ1990ዎቹ ከነበረበት 60 በመቶ ወደ 39 በመቶ ቢቀንስም፣ አሁንም ችግሩ ሙሉ በሙሉ ያልተወገደ መሆኑ ይታወቃል። ይህንን አስከፊ አዙሪት ለመስበር በ2007 ዓ.ም የሰቆጣ ቃል ኪዳን የተሰኘ ታሪካዊ መርሃ ግብር ይፋ ተደርጓል። ይህ ታሪካዊ ቃል ኪዳን በ15 ዓመታት ፍኖተ ካርታ ውስጥ ሦስት ዋና ዋና የትግበራ ምዕራፎችን አካትቶ የያዘ ነው። የመጀመሪያው የኢኖቬሽን ምዕራፍ (2010-2013 ዓ.ም) በ40 ወረዳዎች ላይ ትኩረት በማድረግ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅታዊ አሰራር ውጤታማነት ያረጋገጠበት ሲሆን፣ ቀጥሎ የመጣው የማስፋፋት ምዕራፍ (2014-2018 ዓ.ም) የትግበራ ሽፋኑን ወደ 314 ወረዳዎች አሳድጓል። በዚህ ምዕራፍ በ2017 በጀት ዓመት ብቻ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ህጻናት እና 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን እናቶችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። በአሁኑ ወቅት የተጀመረው የመጨረሻው የማስፋት ምዕራፍ (2019 – 2023 ዓ.ም) ደግሞ የተገኙ ልምዶችን በመቀመር እና ማህበረሰቡን በባለቤትነት በማሳተፍ መቀንጨርን በኢትዮጵያ ዜሮ ለማድረግ የታለመበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ነው። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን፣ ስርዓተ ምግብና ሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የጤና መድህን፣ የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ የ2018 ዓ.ም የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀምን በተመለከተ በበይነ መረብ ውይይት አካሂደው ነበር። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚ ወቅት የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ እድገት መሳካት የጀርባ አጥንት ለሆነው አምራች እና ተመራማሪ ኃይል ግንባታ ያለው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን አንስተዋል። በውይይቱ ላይ ከተነሱት ጉዳዮች አንዱ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ነበር። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ትግበራ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጸው በዚህም በቃል ኪዳኑ የ15 ዓመት ፍኖተ ካርታ መሰረት የመጨረሻው የአምስት ዓመት የማስፋት ምዕራፍ (2019 – 2023 ዓ.ም) የትግበራ ማስፈፀሚያ እቅድ መጽደቁን ጠቅሰዋል። በዚህም የመቀንጨርንና ሌሎች የስርዓተ ምግብ ችግሮች ምጣኔን በፍጥነት ለመቀነስ የተገኙ ልምዶች በመቀመር፣ ማህበረሰቡን በባለቤትነት የማሳተፍ ስራን ማጠናከር እንደሚገባም አንስተዋል። የሰቆጣ ቃል ኪዳን ስኬታማነት ኢትዮጵያ በዓለም ስርዓተ ምግብ ውስጥ ታሪካዊ አሻራ እንድትጥል ከማድረጉም ባለፈ፣ ጤናማ፣ ምርታማና የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የሚገነባ ብቁ ትውልድ ለማፍራት ዋስትና የሚሰጥ ነው። ይህ ጉዞ ከመንግስት የፖለቲካ ቁርጠኝነት ባለፈ፣ መላው ማህበረሰብ እና ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ድጋፋቸውን በማጠናከር ለመጪው ትውልድ የገቡትን የህልውና ቃል ኪዳን በተግባር የሚመሰክሩበት ነው። በአጠቃላይም በአሁኑ ሰዓት የህጻናት መቀንጨርን ለመከላከልም ሆነ አጠቃላይ ምግብን በዓይነትም ሆነ በጥራት በገበታ ሙሉ ለማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት በመላው ሃገሪቱ እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት በዚህ ረገድ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ድህነትን ማሸነፍ ሃገራዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ ግቧ የሆነው ሃገራችን በሁሉም መስክ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት የምግብ ሉዓላዊነቷን በማረጋገጥ የዜጎችን ጤንነት በተሟላ መልኩ ማስጠበቅ የሚያስችላትም ነው።
ባሳለፍነው ሣምንት ...
May 9, 2026 545
ከሚያዝያ 25 እስከ ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … · ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የዘንድሮው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ባሳለፍነው ሳምንት የተከፈተ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ፤ ውጤት ተኮር አመራራችን ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ የኢንዱስትሪ መስፋፋት ተንጸባርቋል ብለዋል። የአምራች ኢንዱስትሪዎች አማካይ የማምረት ዐቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ በማድረግ፣ ባለፉት አራት ዓመታት ከ2 ሺህ 800 በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ተችሏል ብለዋል። ኤክስፖው ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ ንቁ አምራቾችን እና ስታርትአፖችን በጨመረ ዐቅም በአንድነት ማሰባሰቡን ጠቁመው፤ በጋራ በመሆን ይህንን ጠንካራ መነቃቃት በማስቀጠል ለሚመጣው ትውልድ ጽኑ፣ በኢንዱስትሪ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን እንገነባለን ብለዋል። · 85ኛው የጀግኖች ዓርበኞች በዓል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለ85ኛው የጀግኖች ዓርበኞች በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት፤ ሚያዝያ 27 ቀን ኢትዮጵያውያን ጀግኖች ዓርበኞች የፋሽስትን ወረራ የቀለበሱበትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያስከበሩበት በዓል መሆኑን አውስተዋል። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ ዓርበኞችን ይፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የራስ ፍላጎትን፣ ባንዳነትን እና ወራሪን እምቢ የሚል ዓርበኝነት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የኢንዱስትሪ ዓርበኞች፣ የግብርና ዓርበኞች፣ የጸጥታ ዓርበኞች፣ የፖለቲካ ዓርበኞች፣ የንግድ ዓርበኞች፣ የዲፕሎማሲ ዓርበኞች፣ የመንግሥት አገልጋይ ዓርበኞች፣ የሕክምና ዓርበኞች፣ የትምህርት ዓርበኞች፣ ወዘተ. . . ያስፈልጉናል ሲሉም አብራርተዋል። ይህን በዓል የምናከብረው የየራሳችንን የዓርበኝነት ደረጃ በመገምገም ነው፤ በዚህም መሠረት ለኢትዮጵያ ምን ያህል ዓርበኞች ነን? ማለት ይገባናል ብለዋል በመልዕክታቸው። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ዓርበኞቻችን ታሪክ የሠሩት የውስጥ ባንዳንና የውጭ ባዳን ድል ነሥተው ነው፤ እኛም የአባቶቻችን ልጆች በመሆናችን አሁንም ያንን ድል እንደግመዋለን ብለዋል። ዛሬ የዓርበኝነት ትርጉሙ ዘርፈ ብዙ ሆኗል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የዚህ ዘመን ዓርበኝነት በሥራ መትጋትና በዕውቀት መመራት፣ የድህነትን ታሪክ ለመቀየር ቆርጦ መነሣት፣ የተሻለች የነገዋ ኢትዮጵያን በላባችን መገንባት ነው ሲሉም አስረድተዋል። ስለሆነም በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና በዲፕሎማሲ መስኮች ድልን እያስቀጠልን፤ በተደመረ ዐቅም ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ ማማ የሚያወጣ የዘመኑ ዓርበኛ ልንሆን ይገባል ነው ያሉት። · የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጥረት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱልልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሔክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ማሳን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የጀመርነው ጥረት በላቀ ውጤት ቀጥሏል ብለዋል። · የኢትዮጵያና አዘርባጃን ግንኙነት በይበልጥ መጠናከር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ከኔዘርላንድስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮብ ጄተን ጋር ውጤታማ የሥልክ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ መመክራቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚያስችሉ መንገዶች ላይ ሐሳብ ተለዋውጠናል ብለዋል። ·የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት፤ የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ በሚል መሪ ሐሳብ ባለፉት ዓመታት በሚዲያ ዘርፍና ተቋማት ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች የቀረቡበት የምክክር መድረክ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት የሚዲያ ምኅዳሩን በዴሞክራሲያዊ ዐውድ ለመዋጀት በወሰድነው እርምጃ ለሀገር ግንባታ የሚረዳ መሠረት ተጥሏል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ውጤት እንዲቀጥልም ሚዲያዎች ከዋልታ ረገጥነትና ከጽንፈኝነት ወጥተው በእውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት በመገንባት፣ ለጋራ ማንነትና ለብሔራዊ መግባባት በቁርጠኝነት ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። ሚዲያዎቻችን በሰው ሠራሽ አስተውሎት እና በጥናት የታገዘ ጥልቅ ትንተና በማቅረብ፣ ከአርዕስት ሽያጭ ባለፈ ለሀገር አጀንዳዎች ትኩረት መስጠት ይኖርባቸዋልም ነው ያሉት። ተግባራቸውም በዓላማ፣ በዕይታ፣ በሙያዊ ብቃትና ለሕዝብ ቅርብ በመሆን ላይ ተመስርቶ፣ ሚዛናዊነትን በጠበቀ መልኩ ለሀገር ብልጽግና መንገድ ጠራጊና ችግር ፈቺ ሆነው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጂቡቲው ፕሬዚዳንት በዓለ ሢመት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በተመራጩ የጂቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ በዓለ ሢመት ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ወደ ጅቡቲ አቅንተዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባስተላለፉት መልዕክትም፤ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ለሀገራቸው የሚሰጡት አገልግሎት ሁለንተናዊ እድገትን እንዲያስቀጥል ልባዊ ደስታዬንና መልካም ምኞቴን ልገልጽ እወዳለሁ ብለዋል። በኢትዮጵያ እና በጂቡቲ መካከል ያለው የቆየ ወዳጅነት እና ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለሕዝቦቻችን የጋራ ብልጽግና እንዲሁም ለቀጣናችን ሰላምና መረጋጋት መጠናከር መሰረት እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል በመልዕክታቸው። · የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መመረቅ ሪዞርቱ ባሳለፍነው ሳምንት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመረቀ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ለባሕር ዳርና ለአካባቢው ዘርፈ ብዙ ትሩፋት ይዞ የመጣ መሆኑን ተናግረዋል። የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መንግሥት ለቱሪዝም መዳረሻዎች የሰጠው ትኩረት ምን ውጤት እንዳመጣ በገሐድ የሚነበብበት ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው፤ የአካባቢውን የቱሪዝም መሥመርና ሠንሠለት የሚያጠናክር ማረፊያና መዳረሻ ነው ብለዋል። ሪዞርቱ ዘመናዊ እና ቅንጡ የእንግዳ ማረፊያዎች፣ የመዝናኛ ሥፍራዎች፣ ሱቆች፣ አምፊ ቴአትር እና መሰል መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ ጣናን ተንተርሶ የተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል። በተመሳሳይ ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚያው በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ደረጃውን ያሟላ Four Points by Sheraton ሆቴል የግንባታ ፕሮጀክት በይፋ አስጀምረዋል። በርካታ አገልግሎቶችን አሟልቶ በ18 ወራት ግንባታው የሚጠናቀቀው ይህ ሆቴልም የግል ባለ ሀብቱ በሀገራችን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ውስጥ ያለውን ሚና የሚያሳይ ነው ብለዋል። ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በተለያዩ ዘርፎች እያመጣ ያለውን ለውጥ አድንቀው፤ ይህ የሆቴል ግንባታም ለባሕር ዳር በጸጋ ላይ ጸጋ የሚጨምር መሆኑን ተናግረዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ማጠቃለያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሰላፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአራተኛው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ማጠቃለያ ላይ የተመለከትናቸው የጥራትና የፈጠራ ውጤቶች የሀገራችንን የማምረት ዐቅም የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ ታምርት የሉዓላዊነታችን መሠረት የብልጽግናችን ምሦሶ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ ዘርፍ እያሳየችው ያለው ተጨባጭ ዕድገት የብልጽግናችን ማብሠሪያ እየሆነ ይገኛል ሲሉ ገልጸዋል። የሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በምልዓት የሚረጋገጠው በምርት ራስን በመቻል መሆኑን በመገንዘብ የተጀመረው ይህ ንቅናቄ፤ ተኪ ምርትን በማሳደግ፣ የፋብሪካዎችን ዐቅም በመገንባት እና የሥራ ባህልን በመለወጥ ረገድ ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገቡን አስታውቀዋል። መንግሥት ለዘርፉ ምቹ ፖሊሲዎችንና ድጋፎችን ማመቻቸቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠው፤ ቀጣዩን ኤክስፖ ይበልጥ በፈጠራና በስብጥር የላቀ ለማድረግ እንሠራለን ሲሉ አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ
የ471 ሚሊዮን ተከታዮች ባለቤት የሆኑ የ30 ሀገራት ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሳተፉበት ታሪካዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ
May 6, 2026 504
በመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) ላይ ለመሳተፍ፣ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡና በአጠቃላይ 321 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 61 ታዋቂ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ወደ አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። እነዚህንም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 120 ታዋቂ ኢትዮጵያውያን የማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ፈጣሪዎች ይቀላቀሏቸዋል። ታሪካዊው ጉባኤ ነገ እና ከነገ በስቲያ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ጉባኤው በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እና በኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ የጋራ ትብብር የተዘጋጀም ነው። በአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከል አዲስ አበባ የሚካሄደው ይህ ጉባኤ የአፍሪካን ዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ እንደገና ለመቅረጽ ያለመ ነው። ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበር እና የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅበት ስም ነው) ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገብቷል። ሴራሊዮናዊው ቦይዜ ክሪሽ፣ ቤኒናዊቷ ሬጌ ቦይዘር፣ ሴኔጋላዊው ጃው ኬቹፕ እና ስዊዛላንዳዊው ጎጎ እስዋቲኒ ኤምኤም ሌሎች ለጉባኤው የገቡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖፐ ፈጣሪዎች ናቸው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎቹ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል። ጉባኤው በአፍሪካ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሰባሰቡበት፣ ስለራሳቸውና ስለ አፍሪካ የሚናገሩበት፣ እንዲሁም ስለ ይዘት ፈጠራና ስለሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች የሚወያዩበት መድረክ ነው። ይህም ተጽእኖ ፈጣሪዎቹን በአንድ መድረክ የማገናኘት ትልቅ አጋጣሚን ፈጥሯል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በመጠቀም የይዘት ፈጣሪነት የወደፊት ሁኔታ፣ የአፍሪካ አዎንታዊ ገጽታን መገንባት እና የዲጂታል ተጽዕኖን ከአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ጋር ማጣጣም በሚሉ ጉዳዮች ላይ ሶስት የከፍተኛ ደረጃ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ጉባኤው "በችግር ላይ የተመሰረተ" ዘገባን በእውነተኛ የአፍሪካ የዕድገት ታሪኮች ለመተካት የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑም ተመልክቷል። የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ የኢትዮጵያን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ የማስተዋወቅ እድሉ ሰፊ ነው። እነዚህ የይዘት ውጤቶች የአፍሪካን መልካም ገጽታ ለዓለም፣ የኢትዮጵያንም መልካም ገጽታ ለአፍሪካውያን ማሳየት የሚችሉ ናቸው። ጉባኤው ሐሙስ ዕለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚጀመር ሲሆን፣ ከ470 ሚሊዮን በላይ የዲጂታል ተከታዮች አይኖች በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ላይ አርፈዋል። ይህም አፍሪካ የራሷን ታሪክ ራሷ መተረክ የጀመረችበት አዲስ ዘመን ማሳያ ሆኗል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 4945
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 3227
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 9018
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 7502
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 1244
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 1141
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።