ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ድጋፉን እንደሚያጠናክር ገለጸ
Apr 20, 2026 640
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎች ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋገጠ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የፀደይ ወቅት ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ ተካሄዷል። በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ ጋር ውይይት አድርጓል። ሚኒስትሩ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ (Homegrown Economic Reform Agenda) የተመዘገቡ ውጤቶችን ያብራሩ ሲሆን፤ በተለይም በኢኮኖሚ መረጋጋትና በመዋቅራዊ ሽግግር ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን አንስተዋል።   ኢትዮጵያ ወደ ግል ዘርፍ መር የኢኮኖሚ እድገት በምታደርገው ሽግግር፣ የግል ካፒታልን ማሰባሰብ አሁን ላይ ዋነኛው ትኩረት መሆኑን ሚኒስትሩ አፅንኦት የሰጡት ጉዳይ ነው። በተጨማሪም ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት (COP32) ጉባኤን ለማስተናገድ እያደረገችው ስላለው ዝግጅት ለዳይሬክተሩ ገለጻ አድርገዋል። ጉባኤው የኢትዮጵያን የአየር ንብረት መቋቋም አቅምና የአረንጓዴ ልማት ቃል ኪዳኖችን እውን ለማድረግ ያለውን ጉልህ ፋይዳ ጠቁመዋል። የዓለሞ ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ በበኩላቸው የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያደርጋቸውን ድጋፎች ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑንም አመልክተዋል። ዳይሬክተሩ ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 ጉባኤ ዝግጅትም ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። Boost this post to get more reach for Ethiopian News
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው
Apr 20, 2026 295
ቦንጋ ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማሳተፍ የተከናወኑት ተግባራት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ መሆናቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። በክልሉ የመንግስትና የፓርቲ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል ።   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማሳተፍ የተከናወኑት ተግባራት ለህዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ናቸው። በመሰረተ ልማት፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በግብርና፣ በስራ እድል ፈጠራ ፣ በጤና፣ በትምህርትና በሌሎችም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። በክልሉ የተመዘገቡ ልማቶች አበረታች ቢሆኑም ከክልሉ የመልማት አቅም አንፃር ገና ሰፊ ስራ የሚጠይቅ በመሆኑ ይበልጥ መትጋት እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህም የክልሉን አመራሮችና ሰራተኞች እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በማቀናጀት ተከታታይነት ያለው ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባም አክለዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት በመንግስትም ሆነ በፓርቲ የተመዘገቡ ውጤቶችን ማስቀጠል ይገባል ያሉት ደግሞ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን ናቸው።   በተለይም አመራሩ ስራን በመገምገምና በቅንጅት በመስራት እንዲሁም ህብረተሰቡን በማስተባበር የመጡ ውጤቶችን ማስቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገለጹ
Apr 20, 2026 1210
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከኦስትሪያ የአውሮፓ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ሚኒስትር ቢት ሜይንል ራይዚንጀር ጋር ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው የሁለትዮሽን ግንኙነት የበለጠ አጠናክሮ ለመቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።   በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በትምህርት፣ ባህል እና በባለብዙ ወገን ግንኙነት ዘርፍ ጠንካራ ግንኙነት መመሥረት የሚያስችል ገና ያልተነካ የትብብር አቅም እንዳለ አንስተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ለሚኒስትሯ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለውን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማምረቻው ዘርፍ፣ በቱሪዝም እና በዲጂታል መሠረተ ልማት ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች መኖሩን አብራርተዋል። ሚኒስትር ቢት ሜይንል ራይዚንጀር በበኩላቸው ኦስትሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የትብብር መስኮች የማስፋት ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።   በአውሮፓ-ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ላይም የአገራቸው ኩባንያዎች በስፋት መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። ሁለቱ አገራት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም ዓቀፍ የትብብር መድረኮች በተለይም በአየር ንብረት ለውጥ፣ በፍልሰት እና በዘላቂ የልማት ግቦች ዙሪያ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ ለ120 ዓመታት የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አላቸው።
ኢትዮጵያ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየሆነች ነው
Apr 20, 2026 451
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያጠናክሩ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየሆነች ነው ሲሉ የአውሮፓ ሕብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆዜፍ ሲከላ ገለጹ። የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም "ዓለም አቀፍ የገበያ መግቢያ አቅምን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የአውሮፓ ሕብረት ዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆዜፍ ሲከላ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መስራች፣ የቡና መገኛ፣ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነች ታሪካዊ ሀገር ናት።   ኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያጠናክሩ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ መዳረሻዋ የት እንደሆነ በግልጽ አሳይታለች ብለዋል። የአውሮፓ ሕብረት ደረጃቸውን የጠበቁ የመሰረት ልማትና የዲጂታል መሰረተ ልማት ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ሕብረቱ በገጠር መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ ቢዝነስ ፎረም በንግድ ድርጅቶች መካከል፣ በመንግሥት እና በንግድ ድርጅቶች መካከል ገንቢ ውይይት ማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጣ የኢኮኖሚ ሪፎርም ማድረጓንም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። ዛሬ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ከበጀት ድጋፍ ስምምነቱ ባሻገር የ150 ሚሊዮን ዩሮ የዲጂታል ኢኮኖሚ ስምምነት መፈረሙን ገልጸዋል፡፡ ይህም በዲጂታል መሰረተ ልማት፣ ክህሎትና አስተዳደር በጋራ ማዕቀፍ ላይ የተመሰረተ መሆኑን አብራርተዋል።   የአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ዋና ጸሀፊ ዋምኬሌ ሜኔ፤ አፍሪካ ከአራት ሺህ በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎች በመሳተፍ በዓለም ቀዳሚዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህ ትብብር በአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ የተበጣጠሰ የእሴት ሰንሰለት ባለው የዓለም ገበያ በአፍሪካ የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። ኢትዮጵያ የቢዝነስ ስራዎችን የሚያቀላጥፉ የጉምሩክና የፋይናንስ ስርዓቷን እያዘመነች መሆኑን ጠቅሰው፤ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት መፈጠሩን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ትርጉም ያለው ሪፎርም በማድረግ ሀገሪቷን በአፍሪካ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት አድርጓታል ብለዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ቁልፍ የፋይናንስ ተቋማትን አቅም በማጠናከር የተሳለጠ የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል፡፡
የሚታይ
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ድጋፉን እንደሚያጠናክር ገለጸ
Apr 20, 2026 640
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎች ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋገጠ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የፀደይ ወቅት ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ ተካሄዷል። በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ ጋር ውይይት አድርጓል። ሚኒስትሩ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ (Homegrown Economic Reform Agenda) የተመዘገቡ ውጤቶችን ያብራሩ ሲሆን፤ በተለይም በኢኮኖሚ መረጋጋትና በመዋቅራዊ ሽግግር ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን አንስተዋል።   ኢትዮጵያ ወደ ግል ዘርፍ መር የኢኮኖሚ እድገት በምታደርገው ሽግግር፣ የግል ካፒታልን ማሰባሰብ አሁን ላይ ዋነኛው ትኩረት መሆኑን ሚኒስትሩ አፅንኦት የሰጡት ጉዳይ ነው። በተጨማሪም ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት (COP32) ጉባኤን ለማስተናገድ እያደረገችው ስላለው ዝግጅት ለዳይሬክተሩ ገለጻ አድርገዋል። ጉባኤው የኢትዮጵያን የአየር ንብረት መቋቋም አቅምና የአረንጓዴ ልማት ቃል ኪዳኖችን እውን ለማድረግ ያለውን ጉልህ ፋይዳ ጠቁመዋል። የዓለሞ ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ በበኩላቸው የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያደርጋቸውን ድጋፎች ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑንም አመልክተዋል። ዳይሬክተሩ ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 ጉባኤ ዝግጅትም ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። Boost this post to get more reach for Ethiopian News
ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገለጹ
Apr 20, 2026 1210
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከኦስትሪያ የአውሮፓ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ሚኒስትር ቢት ሜይንል ራይዚንጀር ጋር ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው የሁለትዮሽን ግንኙነት የበለጠ አጠናክሮ ለመቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።   በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በትምህርት፣ ባህል እና በባለብዙ ወገን ግንኙነት ዘርፍ ጠንካራ ግንኙነት መመሥረት የሚያስችል ገና ያልተነካ የትብብር አቅም እንዳለ አንስተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ለሚኒስትሯ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለውን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማምረቻው ዘርፍ፣ በቱሪዝም እና በዲጂታል መሠረተ ልማት ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች መኖሩን አብራርተዋል። ሚኒስትር ቢት ሜይንል ራይዚንጀር በበኩላቸው ኦስትሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የትብብር መስኮች የማስፋት ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።   በአውሮፓ-ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ላይም የአገራቸው ኩባንያዎች በስፋት መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። ሁለቱ አገራት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም ዓቀፍ የትብብር መድረኮች በተለይም በአየር ንብረት ለውጥ፣ በፍልሰት እና በዘላቂ የልማት ግቦች ዙሪያ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ ለ120 ዓመታት የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አላቸው።
ኢትዮጵያ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየሆነች ነው
Apr 20, 2026 451
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያጠናክሩ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየሆነች ነው ሲሉ የአውሮፓ ሕብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆዜፍ ሲከላ ገለጹ። የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም "ዓለም አቀፍ የገበያ መግቢያ አቅምን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የአውሮፓ ሕብረት ዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆዜፍ ሲከላ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መስራች፣ የቡና መገኛ፣ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነች ታሪካዊ ሀገር ናት።   ኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያጠናክሩ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ መዳረሻዋ የት እንደሆነ በግልጽ አሳይታለች ብለዋል። የአውሮፓ ሕብረት ደረጃቸውን የጠበቁ የመሰረት ልማትና የዲጂታል መሰረተ ልማት ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ሕብረቱ በገጠር መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ ቢዝነስ ፎረም በንግድ ድርጅቶች መካከል፣ በመንግሥት እና በንግድ ድርጅቶች መካከል ገንቢ ውይይት ማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጣ የኢኮኖሚ ሪፎርም ማድረጓንም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። ዛሬ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ከበጀት ድጋፍ ስምምነቱ ባሻገር የ150 ሚሊዮን ዩሮ የዲጂታል ኢኮኖሚ ስምምነት መፈረሙን ገልጸዋል፡፡ ይህም በዲጂታል መሰረተ ልማት፣ ክህሎትና አስተዳደር በጋራ ማዕቀፍ ላይ የተመሰረተ መሆኑን አብራርተዋል።   የአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ዋና ጸሀፊ ዋምኬሌ ሜኔ፤ አፍሪካ ከአራት ሺህ በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎች በመሳተፍ በዓለም ቀዳሚዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህ ትብብር በአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ የተበጣጠሰ የእሴት ሰንሰለት ባለው የዓለም ገበያ በአፍሪካ የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። ኢትዮጵያ የቢዝነስ ስራዎችን የሚያቀላጥፉ የጉምሩክና የፋይናንስ ስርዓቷን እያዘመነች መሆኑን ጠቅሰው፤ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት መፈጠሩን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ትርጉም ያለው ሪፎርም በማድረግ ሀገሪቷን በአፍሪካ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት አድርጓታል ብለዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ቁልፍ የፋይናንስ ተቋማትን አቅም በማጠናከር የተሳለጠ የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ የአውሮፓ ሕብረትና አባል ሀገራት ኩባንያዎች መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል
Apr 20, 2026 328
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ የአውሮፓ ሕብረትና አባል ሀገራት ኩባንያዎች መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ገለጹ፡፡ የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም "ዓለም አቀፍ የገበያ መግቢያ አቅምን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።   የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ዘላቂ ዕድገት ማስመዝገብ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ ሪፎርም አድርጋለች። ኢትዮጵያ አካታችና ሁሉን አቀፍ ሪፎርም በማድረግ ያላትን ዕምቅ አቅም መጠቀም የሚያስችል ለውጥ እያመጣች መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት ቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያ ያላትን አቅም ለማውጣት፣ ትብብርን ለመፍጠር፣ የገበያ አማራጮችን ለማሰስ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙ የግሉን ዘርፍ በማጠናከር ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንትን መሳብ መቻሉንም ገልጸዋል፡፡ ከሪፎርሙ በኋላ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ጨምሯል፤ የዋጋ ግሽበት ቀንሷል፤ ከወጪ ንግድ የሚገኘው የምንዛሪ መጠን በእጅጉ አድጓልም ብለዋል። ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም በተያዘው ዓመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 9 ነጥብ 2 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘገብ መተንበዩን በመጥቀስ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን በመተግበር ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን እያጠናከረች መሆኑን ገልጸዋል።   መንግሥት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎና የዲጂታል ግብይትን ማጠናከር የሚያስችል የዲጂታል ክፍያና አገልግሎት ስርዓት ማዘመኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በብዝሀ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ተመራጭ መሆኗን በመጥቀስ፣ የአውሮፓ ሕብረትና አባል ሀገራት ኩባንያዎች በኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ በታዳሽ ሀይል፣ ቴክኖሎጂ፣ ጋርመንትና መሰል ዘርፎች መሰማራት ይችላሉ ብለዋል። ለኢንቨስትመንት ምቹ ሥነ ምህዳርና መሰረተ ልማት በመዘርጋት ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆኗን ገልጸዋል። የአውሮፓ ሕብረትና አባል ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ እንደሚችሉ ገልጸው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ለኢንቨስተሮች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነው ብለዋል። የኦስትሪያ ሪፐብሊክ የአውሮፓና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ሚኒስትር ቤአተ ማይነል ረይዚንገር ፤የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጠንካራ የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር የሚፈጠርበት ወቅት መሆኑን ገልጸዋል፡፡   የዓለም ጂኦፖለቲካና ፖሊቲካዊ ሁኔታ ፈታኝ መሆኑን ገልጸው፤ ኦስትሪያ የዓለምን ንግድና ኢንቨስትመንት በር ክፍት ለማድረግ በሚደረገው ጥረት አጋር ለመሆን ዝግጁ ናት ብለዋል፡፡ በኦስትሪያ የኢንዱስትሪ አቅሞችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳደግ እየሰራን ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ ከጣሊያን ጋር በመተባበር ለአየር ንብረት ለውጥ በማይበገር የቡና ምርት የዓለም አቀፍ መግቢያ ፕሮጀክት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በዓለም ልዩ የሆነ የቡና ሥርዓት ዝግጅት እንዳላት ገልጸው፤ በኢ-ተገማች የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ከአጋራ አካላት ጋር ትብብርን ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ተስፋ ያላት ሀገር ናት ያሉት ሚኒስትሯ፤ የኦስትሪያና አውሮፓ ህብረት ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገለጹ
Apr 20, 2026 1210
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከኦስትሪያ የአውሮፓ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ሚኒስትር ቢት ሜይንል ራይዚንጀር ጋር ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው የሁለትዮሽን ግንኙነት የበለጠ አጠናክሮ ለመቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።   በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በትምህርት፣ ባህል እና በባለብዙ ወገን ግንኙነት ዘርፍ ጠንካራ ግንኙነት መመሥረት የሚያስችል ገና ያልተነካ የትብብር አቅም እንዳለ አንስተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ለሚኒስትሯ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለውን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማምረቻው ዘርፍ፣ በቱሪዝም እና በዲጂታል መሠረተ ልማት ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች መኖሩን አብራርተዋል። ሚኒስትር ቢት ሜይንል ራይዚንጀር በበኩላቸው ኦስትሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የትብብር መስኮች የማስፋት ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።   በአውሮፓ-ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ላይም የአገራቸው ኩባንያዎች በስፋት መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። ሁለቱ አገራት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም ዓቀፍ የትብብር መድረኮች በተለይም በአየር ንብረት ለውጥ፣ በፍልሰት እና በዘላቂ የልማት ግቦች ዙሪያ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ ለ120 ዓመታት የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አላቸው።
በጠቅላላ ምርጫው ድምፅ መስጠት የሚያስችለንን ካርድ በመውሰድ ንቁ ተሳትፎ እያደረግን ነው - ወጣቶች
Apr 20, 2026 479
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ካርድ በመውሰድ በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዜጎች ድምፅ መስጫ ካርድ እንዲወስዱ ማራዘሙ ይታወቃል። ሁለት ቀናት በቀሩት የመራጮች ምዝገባም እስከ ሚያዚያ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 46 ሚሊዮን 732 ሺህ 895 መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ተመዝግበዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ አዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች በሰጡት አስተያየት፤ ምርጫ ሕገ መንግስታዊ የመምረጥ መብታችንን ተግባራዊ የምናደርግበት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገለጫ ነው ብለዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሕዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።   ወጣት አቢሲኒያ ተሻለ፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብቱን በመጠቀም ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን የምርጫ ካርድ መውሰዱን ተናግሯል። ወጣት ይበልጣል ባህሩም በተመሳሳይ ሀገራዊ ምርጫ የዴሞክራሲያዊነት መገለጫ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ድምፅ መስጠት የምችልበትን የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ብሏል።   ፋኖስ ታረቀኝ በበኩሏ፤ ምርጫ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተግባራዊ የሚያደርጉበት የአደባባይ መድረክ መሆኑን ገልፃለች።   ካርድ ያልወሰዱ ዜጎችም ቦርዱ የሰጠውን ተጨማሪ የጊዜ ሰሌዳ በመጠቀም ካርድ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርባለች። ጠቅላላ ምርጫው የዜጎችን ዴሞክራሲያዊ ባህል የመገንባት ልምምድ ያጎለብታል ያለው ደግሞ ወጣት ደረጄ ሙሉጌታ ነው።   ለዚህም ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በመውሰድ መዘጋጀቱን አረጋግጧል። ወጣት ታደሰ አያሌው በበኩሉ፤ እንደወጣት የሃሳብ የበላይነት ባህልን በማዳበር በምርጫ ሂደት ገንቢ ሚና የመወጣት ሀገራዊ ኃላፊነት ይጠበቅብናል ሲል ነው የገለጸው።   ለዚህም በምርጫው ወቅት ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በመውሰድ ይበጀኛል ለሚለው ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀቱን ነው የገለጸው።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
Apr 20, 2026 649
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቤይት ሜንለ-ሪዝንገርን ጋር በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በውይይታቸውም በኢትዮጵያና ኦስትሪያ የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ታሪካዊ የዲፕሎማሲና ቀጣይ የትኩረት መስኮች ላይ መክረዋል።   ውይይቱን አስመልክቶ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና የአሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር መለስ ዓለም (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያና ኦስትሪያ ዘመናትን የተሻገረ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው ብለዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቤአተ ማይነል-ረይዚንገር ጋር በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ትብብር ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን ገልጸዋል።   በውይይቱም ፕሬዝዳንት ታዬ በኢትዮ-ኦስትሪያ መካከል የካበተ ታሪክ ያለው ወዳጅነት መኖሩን መግለጻቸውን አንስተዋል። የሀገራቱ ታሪካዊ መልካም ግንኙነትም በዘርፈ ብዙ የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት እየተጠናከረ መምጣቱን ገልጸዋል። የኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቤአተ ማይነል-ረይዚንገር በበኩላቸው፤ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት የበለጠ ለማጠናከር እንደምትሰራ ገልጸዋል ብለዋል።   የኢትዮ-ኦስትሪያን ከ120 ዓመታት በላይ የተሻገረ ታሪካዊ ስትራቴጂክ አጋርነትም በህዝብ ለህዝብ እንዲሁም ጸጥታ ጉዳዮች ለማጠናከር እንደሚሰራ ማረጋገጣቸውን ገልጸዋል። የጉብኝታቸው ዓላማም ከ120 ዓመታት በላይ የተሻገረውን የዲፕሎማሲ ትብብር በሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የበለጠ ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ማንሳታቸውንም ጠቅሰዋል።
ድምጻችን ዋጋ እንዳለው በመረዳት የምርጫ ካርድ ወስደናል
Apr 20, 2026 449
ጅማ ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- ድምጻችን ዋጋ እንዳለው በመረዳት የምርጫ ካርድ ወስደናል ሲሉ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ኢዜአ ያነጋገራቸው የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ድምጻቸው ዋጋ እንዳለው በመረዳት በተሰጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ሄኖክ ወርቁ፤ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና በተለይም አካል ጉዳተኞችን የሚያሳትፍ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። አቶ ሄኖክ አክለውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ወደ ምርጫ ጣቢያቸው በመሄድ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸው እስካሁን ያልወሰዱ ካሉ በቀሪ ቀናት እንዲወስዱም መክረዋል።   አቶ አብዶ አባጊዲ፤ ሁሉንም እኩል ተጠቃሚ የሚያደርግ ለሀገር ለውጥ የሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። "ይህን ማሳካት የምችለው ድምፄ ዋጋ እንዳለው ተረድቼ ካርድ ስወስድ በመሆኑ ቀድሜ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ" ሲሉም አክለዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ ለመምረጥ ካርድ መውሰዷን የገለጸችው ወጣት ሀያት ጣሂር በበኩሏ፤ "የትምህርት ተቋማት ይበልጥ እንዲስፋፉ ስለምፈልግ፣ ይህን ፍላጎቴን የሚያሳካልኝን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ" ብላለች።   ወይዘሮ ፀጋነሽ ግዛውም እንዲሁ የምዝገባው ወቅት ሳይጠናቀቅ ቀድመው ካርድ መውሰዳቸውን ጠቁመዋል።   ህብረተሰቡም የምዝገባው ጊዜ ሳይጠናቀቅ የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ነዋሪዎቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በመደመር እሳቤ የተገኙ ስኬቶችን በማስቀጠል የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Apr 20, 2026 741
ቡታጅራ ፤ሚያዝያ 12/2018(ኢዜአ)፦በለውጡ ዓመታት በመደመር እሳቤ የተገኙ ስኬቶችን በማስቀጠል የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። በለውጡ ዓመታት በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ለተመዘገቡ ስኬቶች እውቅና የሚሰጥ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በቡታጅራ ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በለውጡ ዓመታት የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ባስቀደመ መንገድ በተለያዩ ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን በማከናወን ስኬቶች ተመዝግበዋል። በመደመር እሳቤ የተገኙ እነዚህን ስኬቶችን በማስቀጠል የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ታምርትና ሌሎች ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተከናወኑ ሥራዎች ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በየዘርፉ የህዝብን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግም ለዲጂታል አሰራርና ለወል ትርክት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።   የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በበኩላቸው፥ የብልጽግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካ ፣በማህበራዊና በኢኮኖሚው መስክ በርካታ ስኬቶች ማስመዝገቡን አንስተዋል፡፡ በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሌማት ትሩፋት እና የኢንዱስትሪ ልማት ሥራዎች በቅንጅት መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡
ለሀገራዊ ምክክሩና ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት ሚናችንን እንወጣለን
Apr 19, 2026 2406
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክሩን እና መጪውን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ ለማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የፓርቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮች ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን አቋምና ለምርጫው እያደረጉት ስላለው ዝግጅት አብራርተዋል። የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኦሮሚያ የጋራ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ፤ ‎የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያከናወነ ያለው ተግባር ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት መሠረት የሚሆን ነው ብለዋል።   የኮሚሽኑ የሥራ ዘመን በስምንት ወራት መራዘሙም ኃላፊነቱን በብቃት ለመወጣት እንደሚያስችለው ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ በርሄ በበኩላቸው፣ ምክክሩ ኢትዮጵያውያን የወል ሐሳቦች ላይ መግባባት የሚፈጥሩበት መድረክ መሆኑን ጠቅሰው፣ ሂደቱን በታላቅ ተስፋ እንደሚመለከቱት ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ዋና ጸሐፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ በበኩላቸው፣ ኢዜማ በሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ላይ ንቁና ጠንካራ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቹ ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥና የጋራ መግባባት ለመፍጠር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን በማንሳት ለስኬታማነቱ ሚናቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።   በሌላ በኩል ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረገው ዝግጅት ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እየተከናወነ እንደሚገኝ አመራሮቹ ጠቅሰዋል። የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኦሮሚያ የጋራ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ፥ የሚዲያ ተቋማት ለፓርቲዎች የክርክር መድረክና በቂ የአየር ሰዓት መመደባቸው ለዴሞክራሲ ግንባታ ትልቅ ተስፋ መሆኑን ተናግረዋል። ‎በእጩዎች ላይ የሚደርስ ጫና አለመኖሩና ሂደቱ ሰላማዊ መሆኑ የምርጫውን ተአማኒነት እንደሚያሳድገው የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ በርሄ ናቸው። ‎መንግሥት ለፓርቲዎች እያደረገ ያለው ድጋፍና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መጠናከሩ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታው ስኬታማነት የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። የኢዜማ ዋና ጸሐፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲያቸው በርካታ እጩዎችን በማስመዝገብ ጠንካራ ፉክክር እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ ሕዝቡ በቀሪ ቀናት የምርጫ ካርድ በመውሰድ መብቱን እንዲጠቀም ጥሪ አቅርበዋል። ከሀገርና ከሕዝብ ጥቅም በተቃራኒ መቆም የሕሊናም የታሪክም እዳ መሆኑን ጠቅሰው፥ በሀገር ሉዓላዊነትና በጋራ ጥቅም ጉዳዮች ላይ ከፉክክር ይልቅ ትብብርን እንደሚያስቀድሙ በአፅንኦት ጠቅሰዋል።
ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት የሚቻለው በዜጎች ንቁ ተሳትፎ ነው
Apr 19, 2026 1597
ባህር ዳር፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት የሚቻለው በዜጎች ንቁ ተሳትፎ መሆኑን በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ፡፡ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጩ ህብረተሰብ በቀሩት የምዝገባ ቀናት ካርድ በማውጣት ድምጽ የመስጠት መብቱን እንዲጠቀምም ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል (አዴሃን) ሊቀመንበር አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዜጎች ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነታቸውን የሚያረጋግጡት ይወክለናል የሚሉትን ፓርቲ በመምረጥ በምርጫ መሳተፍ ሲችሉ ነው። የምዝገባ ጊዜው ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ መቅረቱን ያስታወሱት ሰብሳቢው መራጮች በቀሪ ቀናት ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ማውጣት እንዳለባቸው አመልክተዋል። መራጩ ህብረተሰብ የውሳኔ ሰጪነት ዕድሉን ማባከን እንደሌለበት ያስገነዘቡት ሰብሳቢው እድሜያቸው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆኑ ዜጎች በምርጫው በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ መክረዋል። ዴሞክራሲ ቀጣይነት ያለው ሂደት መሆኑን ጠቅሰው ሂደቱ ሰላማዊና ቅቡልነት ያለው እንዲሆን የሁሉንም ህብረተሰብ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ አመልክተዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎችም የምርጫ ቦርድ ያወጣቸውን የስነ-ምግባር መመሪያና ሌሎች ህጎችን አክብረው በመንቀሳቀስ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ አሳስበዋል። የሀገር አንድነትንና ሉዓላዊነትን ከሚጎዱ ተግባራት መቆጠብ እንደሚገባ ጠቁመው በፓርቲዎች መካከል በፖሊሲ ልዩነት ቢኖርም በሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር ላይ ልዩነት መፍጠር አይገባም ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዚያ 14/2018 ዓ.ም መራዘሙን መግለፁ የሚታወስ ሲሆን መራጮችም በቀሪ ጊዜ የመራጭነት ካርድ እንዲወስዱ ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረጉ የተለያዩ ኢንቬቲቮች ተጨባጭ ውጤቶችን አምጥተዋል
Apr 19, 2026 1354
ጅማ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በለውጡ ዓመታት የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረጉ የተለያዩ ኢንቬቲቮች ተጨባጭ ውጤቶች ማምጣታቸውን በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ነመራ ቡሊ ገለጹ። ብልጽግና ፓርቲ በጅማ የምርጫ ምልክትና ማኒፌስቶውን ለህዝብ የማስተዋወቅ መርሃግብር አካሄዷል።   በሁነቱ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ነመራ ቡሊ፣ ባለፉት ዓመታት ዜጎችን ከድህነት በማውጣት ወደ ተሻለ ህይወት ለማሻገር የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በለውጡ ዓመታት የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረጉ የተለያዩ ኢንቬቲቮች ተጨባጭ ውጤቶችን አምጥተዋል ብለዋል። በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚውም ሆነ በማህበራዊ ዘርፎች በመትጋት ዘላቂ ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ እንዲሁም ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማፅናት ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ዘርዝረዋል።   በመደመር እሳቤ ዘመናዊና አሳታፊ የፖለቲካ ስርአት መገንባት ተችሏልም ብለዋል። የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር፣ የጅማ ዞንና ከተማዋ ከለውጡ በፊት ምን ይመስል እንደነበር በማስታወስ ከለውጡ በኋላ የተሰራውን ማየት ለስኬቱ ጥሩ ማሳያ ስለመሆኑ አንስተዋል።   በቀጣይ ይህንን ስኬት ለማስቀጠል ከህዝቡ ጋር በትብብር እንሰራለን ብለዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሃ ቀመር፣ የጅማ ከተማ ልማት ለከተሞች ለውጥና ማንሰራራት ሁነኛ ማሳያ ስለመሆኑ ገልፀዋል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የፓርቲው አመራሮችና አባላት፣ ደጋፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገለጹ
Apr 20, 2026 1210
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከኦስትሪያ የአውሮፓ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ሚኒስትር ቢት ሜይንል ራይዚንጀር ጋር ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው የሁለትዮሽን ግንኙነት የበለጠ አጠናክሮ ለመቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።   በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በትምህርት፣ ባህል እና በባለብዙ ወገን ግንኙነት ዘርፍ ጠንካራ ግንኙነት መመሥረት የሚያስችል ገና ያልተነካ የትብብር አቅም እንዳለ አንስተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ለሚኒስትሯ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለውን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማምረቻው ዘርፍ፣ በቱሪዝም እና በዲጂታል መሠረተ ልማት ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች መኖሩን አብራርተዋል። ሚኒስትር ቢት ሜይንል ራይዚንጀር በበኩላቸው ኦስትሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የትብብር መስኮች የማስፋት ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።   በአውሮፓ-ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ላይም የአገራቸው ኩባንያዎች በስፋት መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። ሁለቱ አገራት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም ዓቀፍ የትብብር መድረኮች በተለይም በአየር ንብረት ለውጥ፣ በፍልሰት እና በዘላቂ የልማት ግቦች ዙሪያ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ ለ120 ዓመታት የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አላቸው።
በጠቅላላ ምርጫው ድምፅ መስጠት የሚያስችለንን ካርድ በመውሰድ ንቁ ተሳትፎ እያደረግን ነው - ወጣቶች
Apr 20, 2026 479
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ካርድ በመውሰድ በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዜጎች ድምፅ መስጫ ካርድ እንዲወስዱ ማራዘሙ ይታወቃል። ሁለት ቀናት በቀሩት የመራጮች ምዝገባም እስከ ሚያዚያ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 46 ሚሊዮን 732 ሺህ 895 መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ተመዝግበዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ አዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች በሰጡት አስተያየት፤ ምርጫ ሕገ መንግስታዊ የመምረጥ መብታችንን ተግባራዊ የምናደርግበት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገለጫ ነው ብለዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሕዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።   ወጣት አቢሲኒያ ተሻለ፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብቱን በመጠቀም ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን የምርጫ ካርድ መውሰዱን ተናግሯል። ወጣት ይበልጣል ባህሩም በተመሳሳይ ሀገራዊ ምርጫ የዴሞክራሲያዊነት መገለጫ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ድምፅ መስጠት የምችልበትን የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ብሏል።   ፋኖስ ታረቀኝ በበኩሏ፤ ምርጫ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተግባራዊ የሚያደርጉበት የአደባባይ መድረክ መሆኑን ገልፃለች።   ካርድ ያልወሰዱ ዜጎችም ቦርዱ የሰጠውን ተጨማሪ የጊዜ ሰሌዳ በመጠቀም ካርድ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርባለች። ጠቅላላ ምርጫው የዜጎችን ዴሞክራሲያዊ ባህል የመገንባት ልምምድ ያጎለብታል ያለው ደግሞ ወጣት ደረጄ ሙሉጌታ ነው።   ለዚህም ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በመውሰድ መዘጋጀቱን አረጋግጧል። ወጣት ታደሰ አያሌው በበኩሉ፤ እንደወጣት የሃሳብ የበላይነት ባህልን በማዳበር በምርጫ ሂደት ገንቢ ሚና የመወጣት ሀገራዊ ኃላፊነት ይጠበቅብናል ሲል ነው የገለጸው።   ለዚህም በምርጫው ወቅት ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በመውሰድ ይበጀኛል ለሚለው ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀቱን ነው የገለጸው።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
Apr 20, 2026 649
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቤይት ሜንለ-ሪዝንገርን ጋር በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በውይይታቸውም በኢትዮጵያና ኦስትሪያ የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ታሪካዊ የዲፕሎማሲና ቀጣይ የትኩረት መስኮች ላይ መክረዋል።   ውይይቱን አስመልክቶ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና የአሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር መለስ ዓለም (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያና ኦስትሪያ ዘመናትን የተሻገረ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው ብለዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቤአተ ማይነል-ረይዚንገር ጋር በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ትብብር ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን ገልጸዋል።   በውይይቱም ፕሬዝዳንት ታዬ በኢትዮ-ኦስትሪያ መካከል የካበተ ታሪክ ያለው ወዳጅነት መኖሩን መግለጻቸውን አንስተዋል። የሀገራቱ ታሪካዊ መልካም ግንኙነትም በዘርፈ ብዙ የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት እየተጠናከረ መምጣቱን ገልጸዋል። የኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቤአተ ማይነል-ረይዚንገር በበኩላቸው፤ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት የበለጠ ለማጠናከር እንደምትሰራ ገልጸዋል ብለዋል።   የኢትዮ-ኦስትሪያን ከ120 ዓመታት በላይ የተሻገረ ታሪካዊ ስትራቴጂክ አጋርነትም በህዝብ ለህዝብ እንዲሁም ጸጥታ ጉዳዮች ለማጠናከር እንደሚሰራ ማረጋገጣቸውን ገልጸዋል። የጉብኝታቸው ዓላማም ከ120 ዓመታት በላይ የተሻገረውን የዲፕሎማሲ ትብብር በሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የበለጠ ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ማንሳታቸውንም ጠቅሰዋል።
ድምጻችን ዋጋ እንዳለው በመረዳት የምርጫ ካርድ ወስደናል
Apr 20, 2026 449
ጅማ ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- ድምጻችን ዋጋ እንዳለው በመረዳት የምርጫ ካርድ ወስደናል ሲሉ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ኢዜአ ያነጋገራቸው የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ድምጻቸው ዋጋ እንዳለው በመረዳት በተሰጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ሄኖክ ወርቁ፤ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና በተለይም አካል ጉዳተኞችን የሚያሳትፍ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። አቶ ሄኖክ አክለውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ወደ ምርጫ ጣቢያቸው በመሄድ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸው እስካሁን ያልወሰዱ ካሉ በቀሪ ቀናት እንዲወስዱም መክረዋል።   አቶ አብዶ አባጊዲ፤ ሁሉንም እኩል ተጠቃሚ የሚያደርግ ለሀገር ለውጥ የሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። "ይህን ማሳካት የምችለው ድምፄ ዋጋ እንዳለው ተረድቼ ካርድ ስወስድ በመሆኑ ቀድሜ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ" ሲሉም አክለዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ ለመምረጥ ካርድ መውሰዷን የገለጸችው ወጣት ሀያት ጣሂር በበኩሏ፤ "የትምህርት ተቋማት ይበልጥ እንዲስፋፉ ስለምፈልግ፣ ይህን ፍላጎቴን የሚያሳካልኝን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ" ብላለች።   ወይዘሮ ፀጋነሽ ግዛውም እንዲሁ የምዝገባው ወቅት ሳይጠናቀቅ ቀድመው ካርድ መውሰዳቸውን ጠቁመዋል።   ህብረተሰቡም የምዝገባው ጊዜ ሳይጠናቀቅ የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ነዋሪዎቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በመደመር እሳቤ የተገኙ ስኬቶችን በማስቀጠል የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Apr 20, 2026 741
ቡታጅራ ፤ሚያዝያ 12/2018(ኢዜአ)፦በለውጡ ዓመታት በመደመር እሳቤ የተገኙ ስኬቶችን በማስቀጠል የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። በለውጡ ዓመታት በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ለተመዘገቡ ስኬቶች እውቅና የሚሰጥ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በቡታጅራ ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በለውጡ ዓመታት የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ባስቀደመ መንገድ በተለያዩ ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን በማከናወን ስኬቶች ተመዝግበዋል። በመደመር እሳቤ የተገኙ እነዚህን ስኬቶችን በማስቀጠል የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ታምርትና ሌሎች ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተከናወኑ ሥራዎች ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በየዘርፉ የህዝብን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግም ለዲጂታል አሰራርና ለወል ትርክት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።   የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በበኩላቸው፥ የብልጽግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካ ፣በማህበራዊና በኢኮኖሚው መስክ በርካታ ስኬቶች ማስመዝገቡን አንስተዋል፡፡ በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሌማት ትሩፋት እና የኢንዱስትሪ ልማት ሥራዎች በቅንጅት መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡
ለሀገራዊ ምክክሩና ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት ሚናችንን እንወጣለን
Apr 19, 2026 2406
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክሩን እና መጪውን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ ለማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የፓርቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮች ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን አቋምና ለምርጫው እያደረጉት ስላለው ዝግጅት አብራርተዋል። የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኦሮሚያ የጋራ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ፤ ‎የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያከናወነ ያለው ተግባር ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት መሠረት የሚሆን ነው ብለዋል።   የኮሚሽኑ የሥራ ዘመን በስምንት ወራት መራዘሙም ኃላፊነቱን በብቃት ለመወጣት እንደሚያስችለው ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ በርሄ በበኩላቸው፣ ምክክሩ ኢትዮጵያውያን የወል ሐሳቦች ላይ መግባባት የሚፈጥሩበት መድረክ መሆኑን ጠቅሰው፣ ሂደቱን በታላቅ ተስፋ እንደሚመለከቱት ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ዋና ጸሐፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ በበኩላቸው፣ ኢዜማ በሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ላይ ንቁና ጠንካራ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቹ ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥና የጋራ መግባባት ለመፍጠር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን በማንሳት ለስኬታማነቱ ሚናቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።   በሌላ በኩል ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረገው ዝግጅት ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እየተከናወነ እንደሚገኝ አመራሮቹ ጠቅሰዋል። የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኦሮሚያ የጋራ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ፥ የሚዲያ ተቋማት ለፓርቲዎች የክርክር መድረክና በቂ የአየር ሰዓት መመደባቸው ለዴሞክራሲ ግንባታ ትልቅ ተስፋ መሆኑን ተናግረዋል። ‎በእጩዎች ላይ የሚደርስ ጫና አለመኖሩና ሂደቱ ሰላማዊ መሆኑ የምርጫውን ተአማኒነት እንደሚያሳድገው የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ በርሄ ናቸው። ‎መንግሥት ለፓርቲዎች እያደረገ ያለው ድጋፍና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መጠናከሩ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታው ስኬታማነት የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። የኢዜማ ዋና ጸሐፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲያቸው በርካታ እጩዎችን በማስመዝገብ ጠንካራ ፉክክር እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ ሕዝቡ በቀሪ ቀናት የምርጫ ካርድ በመውሰድ መብቱን እንዲጠቀም ጥሪ አቅርበዋል። ከሀገርና ከሕዝብ ጥቅም በተቃራኒ መቆም የሕሊናም የታሪክም እዳ መሆኑን ጠቅሰው፥ በሀገር ሉዓላዊነትና በጋራ ጥቅም ጉዳዮች ላይ ከፉክክር ይልቅ ትብብርን እንደሚያስቀድሙ በአፅንኦት ጠቅሰዋል።
ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት የሚቻለው በዜጎች ንቁ ተሳትፎ ነው
Apr 19, 2026 1597
ባህር ዳር፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት የሚቻለው በዜጎች ንቁ ተሳትፎ መሆኑን በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ፡፡ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጩ ህብረተሰብ በቀሩት የምዝገባ ቀናት ካርድ በማውጣት ድምጽ የመስጠት መብቱን እንዲጠቀምም ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል (አዴሃን) ሊቀመንበር አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዜጎች ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነታቸውን የሚያረጋግጡት ይወክለናል የሚሉትን ፓርቲ በመምረጥ በምርጫ መሳተፍ ሲችሉ ነው። የምዝገባ ጊዜው ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ መቅረቱን ያስታወሱት ሰብሳቢው መራጮች በቀሪ ቀናት ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ማውጣት እንዳለባቸው አመልክተዋል። መራጩ ህብረተሰብ የውሳኔ ሰጪነት ዕድሉን ማባከን እንደሌለበት ያስገነዘቡት ሰብሳቢው እድሜያቸው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆኑ ዜጎች በምርጫው በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ መክረዋል። ዴሞክራሲ ቀጣይነት ያለው ሂደት መሆኑን ጠቅሰው ሂደቱ ሰላማዊና ቅቡልነት ያለው እንዲሆን የሁሉንም ህብረተሰብ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ አመልክተዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎችም የምርጫ ቦርድ ያወጣቸውን የስነ-ምግባር መመሪያና ሌሎች ህጎችን አክብረው በመንቀሳቀስ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ አሳስበዋል። የሀገር አንድነትንና ሉዓላዊነትን ከሚጎዱ ተግባራት መቆጠብ እንደሚገባ ጠቁመው በፓርቲዎች መካከል በፖሊሲ ልዩነት ቢኖርም በሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር ላይ ልዩነት መፍጠር አይገባም ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዚያ 14/2018 ዓ.ም መራዘሙን መግለፁ የሚታወስ ሲሆን መራጮችም በቀሪ ጊዜ የመራጭነት ካርድ እንዲወስዱ ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረጉ የተለያዩ ኢንቬቲቮች ተጨባጭ ውጤቶችን አምጥተዋል
Apr 19, 2026 1354
ጅማ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በለውጡ ዓመታት የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረጉ የተለያዩ ኢንቬቲቮች ተጨባጭ ውጤቶች ማምጣታቸውን በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ነመራ ቡሊ ገለጹ። ብልጽግና ፓርቲ በጅማ የምርጫ ምልክትና ማኒፌስቶውን ለህዝብ የማስተዋወቅ መርሃግብር አካሄዷል።   በሁነቱ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ነመራ ቡሊ፣ ባለፉት ዓመታት ዜጎችን ከድህነት በማውጣት ወደ ተሻለ ህይወት ለማሻገር የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በለውጡ ዓመታት የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረጉ የተለያዩ ኢንቬቲቮች ተጨባጭ ውጤቶችን አምጥተዋል ብለዋል። በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚውም ሆነ በማህበራዊ ዘርፎች በመትጋት ዘላቂ ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ እንዲሁም ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማፅናት ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ዘርዝረዋል።   በመደመር እሳቤ ዘመናዊና አሳታፊ የፖለቲካ ስርአት መገንባት ተችሏልም ብለዋል። የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር፣ የጅማ ዞንና ከተማዋ ከለውጡ በፊት ምን ይመስል እንደነበር በማስታወስ ከለውጡ በኋላ የተሰራውን ማየት ለስኬቱ ጥሩ ማሳያ ስለመሆኑ አንስተዋል።   በቀጣይ ይህንን ስኬት ለማስቀጠል ከህዝቡ ጋር በትብብር እንሰራለን ብለዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሃ ቀመር፣ የጅማ ከተማ ልማት ለከተሞች ለውጥና ማንሰራራት ሁነኛ ማሳያ ስለመሆኑ ገልፀዋል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የፓርቲው አመራሮችና አባላት፣ ደጋፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ማህበራዊ
የሹዋሊድ በዓል በዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ለቱሪስት ፍሰት መጨመር የጎላ ሚና አለው
Apr 19, 2026 142
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሹዋሊድ በዓል በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት መመዝገቡ የቱሪስት ፍሰቱን በመጨመር ለሀገር ገፅታ ግንባታ የጎላ ፋይዳ አለው ሲሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ። የሐረሪ ብሔረሰብ በየዓመቱ የሚያከብረው ባህላዊው የሸዋል ኢድ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ ተከብራል። በዚሁ ወቅት ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን እንዳሉት፤ የሸዋል ኢድ በዓል የማኅበራዊ እሴቶቻችንን በማጎልበት አንድነት ይበልጥ እንዲጎለብት ከማስቻሉም ባሻገር በሐረሪ ክልል ያሉ የቱሪዝም ፀጋዎችን በማስተዋወቅ የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ያስችላል።   የሹዋሊድ በተለይም የክልሉ ብሎም የሀገሪቱ የቱሪዝም ዘርፍ እንዲጎለብት ከማድረግ አንፃር የላቀ ጠቀሜታ እንዳለውም ጠቁመዋል። ክልሉ በቱሪዝም ዘርፉ ያለውን እምቅ ዐቅም በመጠቀምም የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።   የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) በሕዳር ቀር 2016 ዓ.ም በቦትስዋና በተካሄደው ስብሰባ የሸዋል ኢድ በዓል አከባበርን በማይዳሰስ የሰው ልጅ ቅርስነት መመዝገቡ ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር የባህልና የወዳጅነት ትስስር የታየበት ነው  
Apr 19, 2026 218
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር የባህል ብልፅግና እና የወዳጅነት ትስስር ጠንክሮ የታየበት ነው ሲሉ የከተማዋ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀፍታይ ገብረእግዚአብሔር ገለጹ። የዓለም አትሌቲክስ የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ የአንድ ቀን ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም በስኬት ትናንት ተካሂዷል።   ውድድሩ መጠናቀቁን ተከትሎም ለተወዳዳሪ አትሌቶች በአራዳ ፓርክ የእራት ግብዣ ተደርጎላቸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀፍታይ ገብረእግዚአብሔር በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ የታሪክ፣ የእንግዳ ተቀባይነት እና የትስስር ከተማ መሆኗን በተግባር አረጋግጣለች። ከተማዋ እንግዶቿን ተቀብላ ከማስተናገድ ባሻገር፣ እንደ ቤታቸው እንዲሰማቸው ማድረጓን ገልጸዋል። ስፖርት የሚጠይቀውን ከፍተኛ ዲሲፕሊንና መስዋዕትነት እንዲሁም የሚፈጥረውን የተስፋ ስሜት ከተማዋ በሚገባ እንደምትረዳም አስገንዝበዋል።   በአዲስ አበባ የተካሄደው ውድድር ከመወዳደሪያነት ባለፈ፣ የወዳጅነት ትስስር የተጠናከረበት፣ የህዝቡ ፍቅር እና የባህል ብልጽግና የታየበት፣ እንዲሁም የከተማዋ ልዩ መንፈስ የተንጸባረቀበት እንደሆነም ጠቁመዋል። አክለውም እንግዶቹ በከተማዋ የሚያሳልፉት እያንዳንዱ ቅጽበት የጋራ ታሪክ አካል እንደሚሆን ገልጸው፤ ቆይታቸው አስደሳች እና የማይረሳ ተሞክሮ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።   የዓለም አትሌቲክስ የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር፣ የኢትዮጵያ አትሌቶች ብቻ የሚሳተፉበት እና ዓለም አቀፍ አትሌቶች የሚሳተፉበት በሚል በሁለት ተከፍሎ ነበር የተካሄደው። የኢትዮጵያ አትሌቶች ብቻ የተሳተፉባቸው የሴቶችና የወንዶች የ10 ሺህ ሜትር፣ እንዲሁም የወንዶች የሦስት ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድሮች ትናንት ከእኩለ ቀን በፊት ተካሂደዋል። በውድድሩም በሴቶች 10 ሺህ ሜትር፡ አትሌት ፋንታየ አዳነ፤ በወንዶች 10 ሺህ ሜትር፡ አትሌት ይስማው ድሉ እና በወንዶች ሦስት ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ገመቹ ጎዳና አንደኛ በመውጣት አሸናፊ ሆነዋል። የዓለም አትሌቲክስ ውድድሩ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ አትሌቶች የተሳተፉበት ከመሆኑም በላይ፣ አሸናፊ ለሚሆኑ አትሌቶች ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከት ተጠቁሟል።
በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው በመመለስ የልማት ተሳታፊ እና ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው 
Apr 19, 2026 90
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-በኢ-መደበኛ ፍልሰት ወደ መካከለኛው ምስራቅና ሌሎች አካባቢዎች ተጉዘው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው በመመለስ፣ በልማት ስራዎች ላይ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ ገለጹ። መንግሥት ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲን በመከተል በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ክብር ለማስጠበቅ ተጨባጭ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ ዜጎች በሕጋዊ መንገድ ተሰማርተው መስራት የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ከተለያዩ ሀገራት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በመፈረም ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን በውጭ ሀገራት መብታቸው ተከብሮ የላባቸውን ዋጋ እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ይሁን እንጂ ሕጋዊ አሰራርን ተከትለው ከመሄድ ይልቅ በኢ-መደበኛ ፍልሰት ከሀገር የሚወጡ ዜጎች መኖራቸውን አስታውሰው፤ ይህም ዜጎችን ለሞት፣ ለአካል ጉዳትና ለሥነ ልቦናዊ ቀውስ የሚዳርግ የተሳሳተ መንገድ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በመካከለኛው ምስራቅና ሌሎች አካባቢዎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት ከመመለስ ባለፈ፣ ማህበራዊ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ እየተደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ተመላሾችን በሀገራቸው ሠርተው እንዲለወጡና የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሥርዓት መዘርጋቱን አንስተዋል። በውጭ ሀገራት ሠርተው የመለወጥ ፍላጎት ያላቸው ዜጎች ራሳቸውን ከተለያዩ ተጋላጭነቶች ለመጠበቅ፣ መንግሥት የዘረጋውን ሕጋዊና መደበኛ የጉዞ ሥርዓት ብቻ ሊከተሉ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ኢኮኖሚ
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ድጋፉን እንደሚያጠናክር ገለጸ
Apr 20, 2026 640
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎች ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋገጠ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የፀደይ ወቅት ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ ተካሄዷል። በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ ጋር ውይይት አድርጓል። ሚኒስትሩ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ (Homegrown Economic Reform Agenda) የተመዘገቡ ውጤቶችን ያብራሩ ሲሆን፤ በተለይም በኢኮኖሚ መረጋጋትና በመዋቅራዊ ሽግግር ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን አንስተዋል።   ኢትዮጵያ ወደ ግል ዘርፍ መር የኢኮኖሚ እድገት በምታደርገው ሽግግር፣ የግል ካፒታልን ማሰባሰብ አሁን ላይ ዋነኛው ትኩረት መሆኑን ሚኒስትሩ አፅንኦት የሰጡት ጉዳይ ነው። በተጨማሪም ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት (COP32) ጉባኤን ለማስተናገድ እያደረገችው ስላለው ዝግጅት ለዳይሬክተሩ ገለጻ አድርገዋል። ጉባኤው የኢትዮጵያን የአየር ንብረት መቋቋም አቅምና የአረንጓዴ ልማት ቃል ኪዳኖችን እውን ለማድረግ ያለውን ጉልህ ፋይዳ ጠቁመዋል። የዓለሞ ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፓስካል ዶኖሆ በበኩላቸው የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያደርጋቸውን ድጋፎች ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑንም አመልክተዋል። ዳይሬክተሩ ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 ጉባኤ ዝግጅትም ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። Boost this post to get more reach for Ethiopian News
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው
Apr 20, 2026 295
ቦንጋ ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማሳተፍ የተከናወኑት ተግባራት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ መሆናቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። በክልሉ የመንግስትና የፓርቲ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል ።   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማሳተፍ የተከናወኑት ተግባራት ለህዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ናቸው። በመሰረተ ልማት፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በግብርና፣ በስራ እድል ፈጠራ ፣ በጤና፣ በትምህርትና በሌሎችም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። በክልሉ የተመዘገቡ ልማቶች አበረታች ቢሆኑም ከክልሉ የመልማት አቅም አንፃር ገና ሰፊ ስራ የሚጠይቅ በመሆኑ ይበልጥ መትጋት እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህም የክልሉን አመራሮችና ሰራተኞች እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በማቀናጀት ተከታታይነት ያለው ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባም አክለዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት በመንግስትም ሆነ በፓርቲ የተመዘገቡ ውጤቶችን ማስቀጠል ይገባል ያሉት ደግሞ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን ናቸው።   በተለይም አመራሩ ስራን በመገምገምና በቅንጅት በመስራት እንዲሁም ህብረተሰቡን በማስተባበር የመጡ ውጤቶችን ማስቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየሆነች ነው
Apr 20, 2026 451
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያጠናክሩ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየሆነች ነው ሲሉ የአውሮፓ ሕብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆዜፍ ሲከላ ገለጹ። የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም "ዓለም አቀፍ የገበያ መግቢያ አቅምን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የአውሮፓ ሕብረት ዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆዜፍ ሲከላ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መስራች፣ የቡና መገኛ፣ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነች ታሪካዊ ሀገር ናት።   ኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያጠናክሩ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመውሰድ መዳረሻዋ የት እንደሆነ በግልጽ አሳይታለች ብለዋል። የአውሮፓ ሕብረት ደረጃቸውን የጠበቁ የመሰረት ልማትና የዲጂታል መሰረተ ልማት ይፈልጋል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ሕብረቱ በገጠር መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ ቢዝነስ ፎረም በንግድ ድርጅቶች መካከል፣ በመንግሥት እና በንግድ ድርጅቶች መካከል ገንቢ ውይይት ማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጣ የኢኮኖሚ ሪፎርም ማድረጓንም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። ዛሬ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ከበጀት ድጋፍ ስምምነቱ ባሻገር የ150 ሚሊዮን ዩሮ የዲጂታል ኢኮኖሚ ስምምነት መፈረሙን ገልጸዋል፡፡ ይህም በዲጂታል መሰረተ ልማት፣ ክህሎትና አስተዳደር በጋራ ማዕቀፍ ላይ የተመሰረተ መሆኑን አብራርተዋል።   የአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ዋና ጸሀፊ ዋምኬሌ ሜኔ፤ አፍሪካ ከአራት ሺህ በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎች በመሳተፍ በዓለም ቀዳሚዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህ ትብብር በአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ የተበጣጠሰ የእሴት ሰንሰለት ባለው የዓለም ገበያ በአፍሪካ የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። ኢትዮጵያ የቢዝነስ ስራዎችን የሚያቀላጥፉ የጉምሩክና የፋይናንስ ስርዓቷን እያዘመነች መሆኑን ጠቅሰው፤ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት መፈጠሩን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ትርጉም ያለው ሪፎርም በማድረግ ሀገሪቷን በአፍሪካ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት አድርጓታል ብለዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ቁልፍ የፋይናንስ ተቋማትን አቅም በማጠናከር የተሳለጠ የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዘመናዊ አሰራሮችን በመተግበር በሀገር ግንባታ ሂደት የበኩሉን እየተወጣ ነው
Apr 20, 2026 271
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዘመናዊ አሰራሮችን በመተግበር በሀገር ግንባታ ሂደት የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) አመለከቱ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የ75ኛ ዓመት የአልማዝ እዮቤልዩ በዓል መክፈቻ ሥነ ሥርዓት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል።   አስተዳደሩ ከምስረታው ጀምሮ አሁን የደረሰበትን ልህቀት ስኬቶችና ተሞክሮዎችን የሚያስቃኝ አውደ ርዕይም በማዕከሉ ተከፍቷል። የተለያዩ ከያኒያንም በዓሉን በማስመልከት ልዩ ልዩ የኪነ ጥበብ ሥራዎችን አቅርበዋል። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አስተዳደሩ በሀገር ግንባታ ሂደት በአርዓያነት የሚጠቀስ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በተቋም ግንባታ በኩልም አስተዳደሩ ምሳሌ የሚሆን ተግባራትን አከናውኗል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ለዘርፉ ዕድገት ጠንካራ የግል ተቋራጭና አማካሪዎች እንዲፈጠሩ የማይተካ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል።   የዘርፉን ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ባለሙያዎችም እንዲበቁ በማድረግ ረገድ ተቋሙ ያከናወናቸው ተግባራትም በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር የመገንባት ሂደቱን ውጤታማ በሆነ መሰረት ላይ እንዲቀመጥ አስችሏል ብለዋል። አስተዳደሩ በቀጣይም ዘመኑን የዋጁ አሰራሮች በመከተልና ጥናትና ምርምሮችን መሰረት በማድረግ ለላቀ ውጤት ሊተጋ እንደሚገባም አመልክተዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን በበኩላቸው፤ አስተዳደሩ ዘመኑን የዋጁ አሰራሮችን በመከተል ብልፅግናን የሚያረጋግጡ ወጤታማ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   ለውጤት የበቁ ዘመናዊ የፍጥነት መንገዶች፣ የተለያዩ ድልድዮች እንዲሁም ተቋሙ የተከተላቸው የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀሞች ለስኬቱ ማሳያዎች ናቸው ብለዋል። የአልማዝ እዮቤልዩ በዓሉ የተሻለች እና ዘመናዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት ቃላችንን የምናድስበት ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የምህንድስናን ጥበብ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። አስተዳደሩ ጥናትና ምርምርን ማዕከል ያደረጉ ሥራዎችንም በሰፊው ገቢራዊ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የመረጃ አያያዝ ስርዓትን በማዘመን ጠንካራ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎትን ለመገንባት ትኩረት ተደርጓል
Apr 20, 2026 87
ባህርዳር ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የመረጃ አያያዝ ስርአትን በማዘመን ጠንካራ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎትን ለመገንባት ትኩረት መደረጉን የአማራ ክልል የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። ‎ቢሮው ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር በመተባበር በሰው ሃብት ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮረ የመረጃ ማረጋገጥ ስራ ላይ ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄዷል። ‎‎የቢሮ ኃላፊዋ ወይዘሮ ባንችአምላክ ገብረማርያም፤ በባህርዳር ከተማ በተካሔደው መድረክ ላይ እንደገለፁት፤ በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎትን ማረጋገጥ ዘርፉን ለማሳደግ ቁልፍ ተግባር ነው።   ‎በተለይም የመንግስት ሰራተኛውን መረጃ በአግባቡ በመለየት፣ በማጥራትና በዘመናዊ መንገድ በማደራጀት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ እንደሚቻልም ነው ያመለከቱት። ‎ይህም የሰራተኛውን አቅም ለመገንባት፣ የደረጃ እድገት ሲሰጥና ጡረታ በሚወጣበት ወቅት የሚያጋጥመውን የመረጃ ክፍተት ለመሙላት እንደሚያስችል ነው ያመለከቱት። ‎በአሁኑ ወቅት የመንግሥት ሠራተኞችን መረጃ ማረጋገጥ እና የሰው ኃይል መረጃን የማዘመን ሥራዎችን ያካተተ ሪፎርም እየተካሄደ መሆኑን ገልፀዋል።   ጥራት ያለው የመንግሥት አገልግሎት ተግባራዊ ለማድረግ አሁን ያለውን የሰው ኃይል፣ ተቋም እና መዋቅር በዲጂታል ሥርዓት መረጃዎችን ማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ቢሮው የመረጃ አያያዝ ስርዓትን በማዘመን ጠንካራ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎትን ለመገንባት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ በከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ሰራተኛውን መረጃ ለማዘመንና ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።   ‎‎መረጃን ማጥራትና ዲጂታላይዝ ማድረጉ የመንግስት ሰራተኛውን አቅም ከመገንባት ባለፈ ጥቅማ ጥቅምን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ አስረድተዋል። ‎‎በተጨማሪም ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊና ተደራሽነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑንም አመላክተዋል። በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የባህር ዳር አገልግሎት ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ሃብታሙ ጤናው በበኩላቸው፤ ትክክለኛ እና ወቅታዊ የሲቪል ሰርቪስ መረጃን ማደራጀት ጊዜው የሚጠይቀው ጉዳይ ነው ብለዋል።   በየደረጃው የሚገኙ ተቋማት የሠራተኞቻቸውን መረጃ በተሟላ መንገድ በመያዝ ለዲጂታል ሥርዓት ሽግግር የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡም ነው ጥሪ ያቀረቡት።‎ ‎በአሁኑ ወቅትም በወረቀት የሚገኙ ፋይሎችን ወደ ዲጂታል ለመቀየር እስከ ወረዳ ለሚገኙ የሲቪል ሰርቪስ የሰው ሃብት ልማት ዳይሬክተሮች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል ነው ያሉት። የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑት አቶ ደሳለኝ አገኘ እንዳሉት፤ የሲቪል ሰርቪሱን መረጃ በማጥራት ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተቀመጠው አቅጣጫ የሰራተኛውን መብትና ጥቅም ለማስከበር የሚያስችል ነው ብለዋል። ‎ስልጠናው በባህር ዳር፣ በጎንደር፣ በኮምቦልቻና ደብረ ብርሃን ከተሞች መሆኑን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ሀገር አቀፍ ጥናቱ ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ለመገንባት መሰረት ይጥላል
Apr 20, 2026 90
ድሬዳዋ፤ሚያዝያ 12/2018(ኢዜአ)፦የመንግስት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ ሀገር አቀፍ ጥናት ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ለመገንባት መሰረት እንደሚጥል የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ገለፀ። ለድሬዳዋ አስተዳደርና ለሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች የመንግሥት ሠራተኞች የፐርሶኔል መረጃ ማጥራትና ማረጋገጥ ጥናቱን ለመተግበር የሚያስችላቸው ስልጠና ዛሬ ተሰጥቷል።   በስልጠናው ላይ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ግርማ ፤ እንደ ሀገር የሚካሄደው የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ ጥናት የሰው ኃይል ስራ አመራርን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል። ጥናቱ ትክክለኛ መረጃን በማረጋገጥና የተቋማትን የመረጃ አያያዝ ክፍተት በመሙላት የሰው ሃብት የመረጃ አያያዝን ዲጂታላይዝ ማድረግ እንደሚያስችል ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ጥናቱ ወደ ዘመናዊ እና አውቶሜትድ የሰው ሃይል ስራ አመራር ስርአት ለመሸጋገር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ነው አቶ ሙሉጌታ የገለፁት። ለጥናቱ መሳካት አስፈላጊው ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ ወር መጨረሻ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት ጥናቱ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር የሲቪል ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሰቦ አህመድ በበኩላቸው፤ ሀገር አቀፉ ጥናት ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ በመፍጠር የህዝብን መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በላቀ ተጠያቂነት እና ግልፀኝነት ለመፈፀም ቁልፍ አበርክቶ እንዳለው አንስተዋል።   በሚሰበሰበው ትክክለኛ መረጃ ላይ በመመስረት ሠራተኞች ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች መንግስት በፍጥነት ምላሽ ለመስጠትና ሠራተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል። በተጨማሪም ሙስናና ብልሹ አሠራሮችን በማስወገድ ከሰው ንክኪ የፀዱ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ የመንግስትና የህዝብ ሃብት ከብክነት ለመከላከል ሚናው የጎላ መሆኑን አስታውቀዋል። ጥናቱ እንደ ሀገር የተጀመሩትን ውጤታማ የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጦችን በማላቅ የብልጽግና ጉዞን ይበልጥ ለማፋጠን ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው የገለፁት ደግሞ የሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ አብዱረህማን ናቸው።   አቶ መሐመድ አክለውም፤ ለጥናቱ መሳካት የተመደቡ አስተባባሪዎች ፣ የተቋማት የሰው ሃብት ስራ አመራር ባለሙያዎች እና ኃላፊዎች በላቀ ቁርጠኝነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ ዲጂታላይዝ ማድረግ ፈጣን አገልግሎትን ለመስጠት ያስችላል
Apr 20, 2026 107
ደብረ ብርሃን/ኮምቦልቻ፤ሚያዝያ 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ ዲጂታላይዝ የማድረግ ተግባሩ ፈጣን አገልግሎትን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ ⵆ ቢሮው ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች የመረጃ ማረጋገጥ ሥራን የተመለከተ የምክክር መድረክ በደብረ ብርሃንና ኮምቦልቻ ከተሞች አካሄዷል። የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአደረጃጀት ስራ ምዘናና ክፍያ ጥናት ዳይሬክተር አቶ አንተነህ ይስማው፤ በደብረ ብርሃን መድረክ እንደገለጹት የዲጂታላይዜሽን ትግበራው የሲቪል ሰርቪስ ግንባታን ለማፋጠን የሚያስችል ነው። ይህም የመንግስት ሰራተኛውን በጠራ መረጃ ላይ በመመስረት መብትና ጥቅሙን በፍትሃዊነት በማሳደግ የስራ ተነሳሽነቱን ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ስርዓቱ ህግ አውጪና ህግ አስፈፃሚ አካላት በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርተው እንዲወስኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።   የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ካሱ አበባው፤ በኮምቦልቻ ከተማ በተካሄደው መድረክ ላይ እንደገለፁት፣ የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ በማጥራትና ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተሰራ ነው።   በክልሉ የሚገኙ ከ560 ሺህ በላይ የመንግስት ሰራተኞችን በመረጃ አያያዝ ስርዓት ወደ አንድ ቋት በማስገባት ፈጣንና ተደራሽነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት መደረጉን አንስተዋል። መረጃውን ዲጂታላይዝ የማድረግ ጥረቱ በአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ መሰረት የሰራተኞችን መረጃ በማጥራት ፍትሃዊ የደሞዝ ጭማሪ፣ የደረጃ እድገትና ምደባ በመስጠት መብትና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ያስችላል ብለዋል። በተጨማሪም ተጠያቂነት ያለው፣ ፈጣንና ፍትሃዊ አገልግሎት ለህብረተሰቡ በመስጠት የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ዓይነተኛ ሚና እንደሚኖረውም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የደሴ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኡስማን መሀመድ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከግንቦት ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ወራት የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ የማጥራት ስራ ይሰራል።   በዚህም ለመረጃ ሰብሳቢዎችና ለባለድርሻ አካላት ስልጠና በመስጠት ግንዛቤ መፈጠሩን ጠቁመው፣ መረጃውን በጥንቃቄ በመያዝ ወደ ሲስተም ለማስገባትና ዲጂታል ለማድረግ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። ቆጠራው በስራ ላይ የሌሉ ሰራተኞችን ለመለየት፣ ከአንድ ተቋም በላይ የሚሰሩትንና የሰራተኞችን የትምህርት ደረጃ ለመለየት ለቀጣይ ስራ ዝግጁ ለማድረግ እንደሚረዳም ተናግረዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በሪሁን ተገኝ በበኩላቸው፤መረጃ ለማጥራት የሚያስችሉ ባለሙያዎች ተለይተው ቴክኒካል ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን ጠቁመዋል።   በከተሞቹ በተካሄዱ መድረኮችም ከፌዴራል፣ ከክልል፣ ከዞን፣ ከከተማና ከወረዳ የተውጣጡ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ስፖርት
ወላይታ ድቻ ድል ሲቀናው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጵያ መድን ነጥብ ተጋርተዋል 
Apr 20, 2026 94
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መካሄዳቸውን ቀጥለዋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ምድረ ገነት ሽሬን 1 ለ 0 ረትቷል። ያሬድ ዳርዛ በ64ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በሊጉ ሰባተኛ ድሉን ያስመዘገበው ወላይታ ድቻ በ34 ነጥብ ደረጃውን ከ16ኛ ወደ 10ኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 11ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ምድረ ገነት ሽሬ በ29 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ሰባት የሊግ ጨዋታዎች ከድል በመራቅ የውጤት ማጣት ቀውስ ውስጥ ይገኛል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ሌላኛው ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጵያ መድን አንድ አቻ ተለያይተዋል።   በዛብህ መለዮ በ67ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ ኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪ ሆኗል። ይሁንና አማኑኤል ኤርቦ በ84ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፈው ጎል ለኢትዮጵያ መድን አንድ ነጥብ አስገኝታለች። ሀሰን ሁሴን ከኢትዮ ኤሌክትሪክ፣ አብዱል ጋንዩ ከኢትዮጵያ መድን በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥተዋል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ42 ነጥብ ደረጃውን ከስድስተኛ ወደ አምስተኛ ከፍ አድርጓል። ኢትዮጵያ መድን በ31 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። የወቅቱ የሊጉ የዋንጫ ባለቤት ኢትዮጵያ መድን ባለፉት አራት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። በተመሳሳይ ዛሬ በተደረገ የ28ኛ ሳምንት ጨዋታ ሸገር ከተማ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል።
በሐረሪ ክልል ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ ነው
Apr 20, 2026 176
ሐረር ፤ሚያዚያ 12/2018 (ኢዜአ) ፡-በሐረሪ ክልል በስፖርት ዘርፍ በሚከናወኑ ስራዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታ እየተፈጠሩ መሆኑን የስፖርት ቤተሰቦች ገለጹ። በክልሉ ‎የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ልማትና የፕሮጀክት ስልጠናዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑ ተመላክቷል ።   በክልሉ የሐረር ጀጎል እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ አክረም መሀመድ ለኢዜአ እንደገለጸው በክልሉ ከዚህ ቀደም ተተኪ ስፖርተኞችን የማፍራትና የድጋፍና እገዛ ተግባራት ትኩረት ተነፍጎት ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት ህፃናትና ታዳጊዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁሞ ለዘርፉ ስልጠና የተሰጠው ትኩረት አሰልጣኞችንም እያበረታታ መሆኑን አመልክቷል ። በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የስፖርት መሰረተ ልማት ግንባታና የድጋፍ ስራዎች ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊዎችን ወደ ስፖርቱ ለመምጣት ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ ነው ያሉት ደግሞ የታዳጊ ፕሮጀክት እግር ኳስ አሰልጣኝ ኢንስፔክተር ፈይሰል መሀመድ ናቸው።   በተለይ ቀደም ሲል እንደ ችግር ሆኖ ጥያቄ ሲቀርብባቸው የነበሩ ተቀራርቦ የመስራት ተግዳሮቶችን ለመፍታት በተከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም የቅንጅት ስራዎች እየጎለበቱ በመሆኑ ተተኪ ስፖርተኞችን የማፍራት ተግባራትን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ አመላክተዋል። የታዳጊ ፕሮጀክት ሰልጣኝ የሆነው ማስተዋል ታጠቅ በበኩሉ “በከተማው ከኮሪደር ልማት ጋር በማስተሳሰር በየአካባቢው የተከናወኑ የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራዎች ተሰጧችንን ለማውጣት እድል እየፈጠሩልን ነው ብሏል። በተለይ በታዳጊዎች ፕሮጀክት ታቅፈን የሚሰጠን ስልጠና ወደፊት ታላላቅ ክለቦች ላይ መሳተፍ የሚያስችለን ክህሎት እየወሰድን እንገኛለን ፤ እኛም ደግሞ በተገቢው መንገድ እየሰራን እንገኛለን ሲል ገልጿል።   በክልሉ ለታዳጊ ፕሮጀክት ስልጠና እየተደረገ የሚገኘው ድጋፍና በየአካባቢው የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራ ግንባታ ተስፋ የሚሰጡ ስራዎች ሆነው አግኝተናቸዋል ያለው ሌላው የታዳጊ ፕሮጀክት ሰልጣኝ አብረሃም አሸናፊ ነው። እኛም የነገዋ ኢትዮጵያ የምትጠብቅብንን አሸናፊነት ለማምጣት ከወዲሁ ተግተን እየሰራን እንገኛለን ብሏል የሐረሪ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙራድ አብዲ በበኩላቸው በክልሉ ‎የስፖርት ማዘውተሪያ ስራዎችን የማልማትና ፋሲሊቲዎችን በማሟላት ተተኪ ስፖርተኞችን የማፍራት ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።   በዚህም የክልሉ መንግስት ቀደም ሲል የነበሩ የማዘውተርያ ስፍራዎችን የማዘመን እንዲሁም በየወረዳው አንድ የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራ የመገንባት ስራ በእቅድ ይዞ እያከናወነ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል። እግር ኳስን ጨምሮ በሁሉም የስፖርት ዓይነቶች ክልሉን ብሎም ሀገርን ወክለው በዓለም አቀፍ መድረክ የሚወዳደሩ ስፖርተኞችን ማፍራት የሚያስችሉ የታዳጊ ፕሮጀክት ስልጠናዎች አዲስ ፎርማት ተቀርጾላቸው ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አመልክተዋል።  
አካባቢ ጥበቃ
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች የዝናብ ቀጣይነት ይኖራል
Apr 20, 2026 77
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የዝናብ ቀጣይነት እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ከሚቲዎሮሎጂ ክስተቶች ጋር ተያይዞ ወቅታዊ ዝናብ ቀስ በቀስ ወደ ምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተስፋፋ እንደሚሄድ ገልጿል። በዚህም በደቡብ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ምስራቅ እንዲሁም በስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች የተሻለ ገጽታ ይኖራቸዋል ብሏል። በመሆኑም በበልግ አብቃይ አካባቢዎች በርካታ ቦታዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በውሃ አካላትና በአካባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በመነሳት በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ ብሏል። አርሶ እና አርብቶ አደሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት የሚጠበቁ መልካም ሁኔታዎችን በአግባቡ እንዲጠቀሙና የግብርና ተኮር ሚቲዎሮሎጂ ምክረ ሀሳቦችን መተግበር እንደሚገባ አስታውቋል። ይህም ለበልግ ሰብሎች እና ቋሚ ተክሎች እድገት አዎንታዊ ሚና ያለው ሲሆን ለአፈር እርጥበት በመጨመር ለእርሻ እንቅስቃሴ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው ያለው። በሚቀጥሉት አስር ቀናት በአብዛኞቹ የሀገሪቱ ተፋሰሶች ላይ የሚጠበቀው ዝናብ የገጸ ምድር ውሃ ፍሰትን እንደሚያሻሽልም ጠቁሟል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን በአረንጓዴ አሻራው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው አገር በቀል ችግኞች ተዘጋጅተዋል
Apr 20, 2026 107
ደብረ ማርቆስ፤ሚያዚያ 12/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ጎጃም ዞን በአረንጓዴ አሻራ የሚተከሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው አገር በቀል ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን የምስራቅ ጎጃም ዞን የተፈጥሮ ሃብት መምሪያ አስታወቀ። በአረንጓዴ አሻራው የሚተከሉት ችግኞችም የተለያዩ ዝርያ ያላቸው መሆኑን በመምሪያው የተፈጥሮ ሃብት ቡድን መሪ አቶ ንጉሴ ሽመልስ ለኢዜአ ገልጸዋል። በዘንድሮው ዓመት በአረንጓዴ አሻራና በመደበኛው የክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ52 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን የተራቆተ መሬት ላይ ችግኞች እንደሚተከሉም ነው ያስረዱት። ከተዘጋጁት ችግኞች ውስጥም የኮሶ፣ የግራር፣ የወይራ፣ የጌሾ፣ የዋንዛ፣ የባህር ዛፍ፣ የሳስቫኒያ፣ የዲክረንስ፣ የፈረንጅ ጽድና ሌሎች የችግኝ ዓይነቶች እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። ችግኞቹን ማዘጋጀት የተቻለውም ከ38 ሺህ በላይ በሚሆኑ የመንግስት፣ የማህበራትና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መሆኑንም ነው ያስታወቁት። እንደ መምሪያው ገለጻ፥ በበጀት ዓመቱ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ከ261 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ተከናውኗል።
በምስራቅ ቦረና እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም የችግኝ ተከላ እየተከናወነ ነው
Apr 20, 2026 107
ነገሌ ቦረና፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ፡- በምስራቅ ቦረና ዞን እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተከላ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ። በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ አቶ አልዬ አረባ ፤በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች ከ32 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለማፍላት ታቅዶ ሲሰራ ቆይቷል። እስካሁን በተካሄደው እንቅስቃሴ ድርቅንና የአካባቢ መራቆትን በመቋቋም ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የሚያስገኙ ከ25 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለማዘጋጀት መቻሉን ገልጸዋል፡፡ ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል የደን ዛፍ፣ የተለያዩ ፍራፍሬዎች እና የእንስሳት መኖ የሚሆኑት ዋነኞቹ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የተዘጋጁት ችግኞች በዞኑ ቆላማ ወረዳዎች ከመጋቢት አጋማሽ እስከ ሚያዝያ መጨረሻ ድረስ የሚጥለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም የሚተከሉ መሆኑን ተናግረዋል። እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀምም እስካሁን በ 2 ሺህ 83 ሄክታር መሬት ላይ ችግኞች መተከላቸውንም ነው ያስታወቁት። በችግኝ ተከላው በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ የተራቆተ ከ7 ሺህ 600 ሄክታር በላይ መሬት በመከለል ለማልማት ትኩረት መሰጠቱን አመላክተዋል። በዘላቂ ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተካሄደ ባለው የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ከ159 ሺህ በላይ ህዝብ እየተሳተፈ መሆኑንም ጠቁመዋል። በዞኑ እየተስፋፋ የመጣው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየዓመቱ የሚከሰተውን ድርቅና የአካባቢ መራቆት ለመከላከልና ለመቋቋም ማስቻሉን አክለዋል። መርሃ ግብሩ ለዞኑ ህዝብ መሰረታዊ ችግር የነበረውን የመጠጥ ውሀና የእንስሳት መኖ እጥረት እያቃለለ መምጣቱንም ጠቅሰዋል። በዚህም በየዓመቱ ለዞኑ ህዝብ ከመንግሥት ሲቀርብ የነበረው የመጠጥ ውሀና የእንስሳት መኖ ድጋፍ ሙሉ ለሙሉ ለማስቀረት ማስቻሉን አብራርተዋል። በዝናብ አጠርና ቆላማ ወረዳዎች የተጀመሩት የበጋ መስኖ፣ የተፋስስ ልማትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተግባራት የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ ሁለንተናዊ እገዛ ማድረጋቸውን አብራርተዋል።    
ኮፕ 32 ዘላቂ ትሩፋት ያለው ሆኖ እንዲያልፍ ለማድረግ ይሰራል - ዓለምጸሐይ ጳውሎስ
Apr 18, 2026 195
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ32) ሂደት ዘላቂ የሆነ ትሩፋት ያለው ሆኖ እንዲያልፍ ለማድረግ እንደሚሰራ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሐይ ጳውሎስ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ32) ብሔራዊ ኮሚቴ የተከናወኑ ሥራዎችን ገምግመዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሐይ ጳውሎስ በዚሁ ወቅት የኮፕ32 መሠረተ ልማት፣ ሎጂስቲክስ እና ኦፕሬሽን ግብረ ኃይል የተከናወኑ ተግባራትን እና ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮችን በሚመለከት ለኮፕ32 ‎ብሔራዊ ኮሚቴ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡   በማብራሪያቸውም የግብረ ኃይሉ ዓላማ ጉባዔው ከመካሄዱ በፊት አስፈላጊ የሆኑ ጉዳዮችን በማሟላት፤ ጉባዔው በሚካሄድበት ወቅት የተሳለጠ እንዲሆን እንዲሁም ከተጠናቀቀ በኋላ ትውልድ ተሻጋሪ የሆነ ዕሴት አሳርፎ ማለፍ እንዲችል ማድረግ ነው ብለዋል። በዚህም ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና መስፈርቶችን የሚያሟሉ መሠረተ ልማቶች የሚገነቡ እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚሰባሰቡ አስፈላጊ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቁመዋል። ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ የተሳለጠ እና ስኬታማ ጉባዔ ከማካሄድ በተጨማሪ ወደ ትውልድ መሻገር የሚችሉ፣ ዘላቂ እና ለቀጣይ ስራዎች አጋዥ የሚሆኑ መሠረተ ልማቶች መገንባትን ታሳቢ ያደረገ ዓላማን በመያዝ እየተሰራ ነው ብለዋል። ግብረ ኃይሉ መሠረታዊ የሚባሉ ግቦችን በመለየት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸው፤ የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟሉ እና ጉባዔውን የሚያሳልጡ መሆናቸውን ማረጋገጥ የመጀመሪያው ግብ መሆኑን አመላክተዋል። የተገነቡ መሠረተ ልማቶች እንግዶች በጉባዔው ለመሳተፍ ሲመጡ ከአቀባበል ጀምሮ እስከሚሸኙበት ጊዜ ድረስ ደረጃውን የሚመጥን እንቅስቃሴዎች እንዲኖሩ በማድረግ ስኬታማ ጉባዔ እንዲካሄድ መሠረታዊ ጉዳዮችን የያዘ መሆኑን ተናግረዋል።   በዚህ ሂደት ነባሩ የከተማ እንቅስቃሴ እና የሕብረተሰብ አገልግሎት እንደተጠበቀ ሆኖ ነባሩን ሳይረብሽ አዲስ የሚመጣውን መቋቋም የሚችል የማይበገሩ መሠረተ ልማቶች መኖራቸውን የማረጋገጥ ግብ ሌላኛው ትኩረት የተደረገበት እንደሆነ መግለጻቸውን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል። በሂደቱ የሚፈጠሩ አቅሞች በተለይም ወጣቶች በሂደት ውስጥ እንዲያልፉ በማድረግ የሀገር ውስጥ አቅምን መገንባት የሚያስችል ስራ እንደሚሰራም አብራርተዋል። በተጨማሪም ሙሉ ሂደቱ ዘላቂ የሆነ ትሩፋት ያለው ሆኖ እንዲያልፍ ማድረግን ታሳቢ በማድረግ እንደሚሰራ ገልጸው፤ ጉባዔው ከተለያዩ ጉዳዮች አኳያ ደኅንነቱ የተጠበቀ ሆኖ እንዲካሄድ የሚያስችል ግቦችን በመያዝ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 459
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 371
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 659
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት።   ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።   የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው 
Mar 22, 2026 352
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 19, 2026 308
የምግብ ሉዓላዊነት - ከተረጂነት መላቀቂያው መንገድ በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ ከተረጂነትና ጠባቂነት መፋቻ መንገዶች መካከል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አንዱ ብልኀት አድርጋ እየታተረች ነው። ይህን ተከትሎም የዜጎችን የምግብ ፍላጎት በራስ የምርት ዐቅም የመሸፈን ሥራ በመከወን ከጠባቂነት ለመላቀቅ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ስኬታማ ናቸው። ለዚህም ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ከልመና ወጥታ ወደ ውጭ ገበያ መላክ መጀመሯ አሥረጅ ነው። በመሆኑም ከውጭ የኢኮኖሚ ጥገኝነት በመላቀቅ የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት ለማስከበር በስንዴ ልማት የተመዘገበውን ስኬት በሌሎች የግብርና ዘርፎች ለመድገም ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም መሠረት በሩዝ፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ሻይ ቅጠል እና ሌሎች የተለያዩ ሰብሎች ላይ እየተከናወነ ያለው ሥራ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው። የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የግብርና ድርጅት (ፋኦ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምግብ ዋስትናና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ የአመራር ቁርጠኝነት የአግሪኮላ ሜዳሊያ በ2016 ዓ.ም ማበርከቱ ለምግብ ሉዓላዊነት ጥረት የተሰጠ ዕውቅና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ረሃብን ከማስቀረት ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ብሔራዊ ብልጽግናን ዕውን ለማድረግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሃብቶች፣ተስማሚ የዓየር ንብረት፣ ለሥራ ትጉ የሆነ ወጣት እንዳላት እና እነዚህን ሃብቶች ታሳቢ በማድረግ የታሪክ ዐውራ የሆነችውን ሀገር ልማት ወደፊት ለማራመድ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ እንደከፈልን ሁሉ፤ ከምግብ ጥገኝነት ለመላቀቅ በትጋት መሥራት ይገባል ሲሉ ማስገንዘባቸው ይታወሳል። የምግብ ሉዓላዊነት፣የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት፣ የበጀት ሉዓላዊነት ታላቁን የሀገር ሉዓላዊነት በጽናት የሚያቆሙ መሆናቸውንም አብራርተዋል። እነዚህን የሉዓላዊነት ዘርፎች ለማስከበርም ብሔራዊ ዐርበኝነት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። ሀገራዊ ትልሙ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት የሚያሸጋግር መልካም ጅማሮ ነው።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 19, 2026 136
ክልሎች፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የንፋስ ሃይል በቀጥታ የምናመራው በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ ነው። በኢተያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው የመረቁትን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን እንመለከታለን። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 100 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል ልማት ወደ ፊት እየተራመደች መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ሥራ ነው። ኢትዮጵያ ዘንድሮ ከጉባ እስከ አሰላ፣ ገናሌ እና አይሻ በሃይል ልማት ዘርፍ ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ፕሮጀክቶች አስመርቃለች። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ደግሞ በዚህ ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀምሯል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩም በምርቃቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ከለውጡ በፊት የነበረው 4 ሺህ ሜጋ ዋት የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በመድረስ ከእጥፍ በላይ እድገት የተመዘገበበትን ትልቅ ስኬት አንስተዋል። የስንዴና ገብስ ሰብሎችን በከፍተኛ መጠን የሚያመርተው አርሲና አካባቢው አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ሃይል የሚመረትበት አካባቢ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እናስቀጥላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። ቢሾፍቱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማም በዚህ ሳምንት በቢሾፍቱ ሀርሰዴ አዳራሽ መካሄዱ ይታወቃል። በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ስኬታማ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይም የክልሉን ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ የከተማ እና የገጠር የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ነው ያስረዱት።   ከዚህ ባለፈ የክልሉን የልማት ሥራዎች ለማቀላጠፍ የሚያግዙ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የአገልግሎት አሰጣጥ አሰራሮች መተግበራቸውንም ተናግረዋል። የቢሾፍቱ መድረክ በድምሩ የግብርና፣ የገጠርና የከተሞች ልማት፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ክንውን በዝርዝር የታየበት ውጤታማ መድረክ እንደነበረም ተመላክቷል። የአሎማ ክላስተር ሌላ የሳምንቱ ዓበይት ጉዳይ ወደ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ይወስደናል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በይፋ አገልግሎት መስጠት የጀመረው በዚህ ሳምንት ነው። በመስኖ የለማ የስንዴ ክላስተር የተጎበኘበትና በተሁለደሬ ወረዳ በክላስተር ለሚከናወነው የተቀናጀ የፍራፍሬ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ የተጀመረበት እንዲሁም የክልሉ የ10 ዓመት የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገበትን ሁነት እናገኛለን።   በእነዚህ ሁነቶች ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የመደመር መንግሥት በሁሉም ዘርፎች ለሀገር እድገትና ማንሰራራት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም በግብርና፣ በመስኖ ልማት፣ በቱሪዝምና ሌሎች መስኮች በተግባር የተመለከትናቸው የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። የአሎማ ክላስተር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የሓይቅ ዳር አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የማቻል ጥረት በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን የሚያሳዩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሀገርን የማሻገር ሥራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የታሪክ መሰነጃ የሳምንቱ በረራችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ የሰው ልጅ መገኛ፣ የኤርታሌ ትኩሳት የሚገነፍልባትና የአዋሽ ወንዝ የተንጣለለባት አፋር ክልል ገብተናል። በአፋር ቆይታችን ትኩረታችንን ሰመራ በማድረግ በስፍራው ሊገነባ የታሰበውን የሉሲ ሙዚየም እንመለከታለን። ሙዚየሙን ለመገንባት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እና የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ የፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት አድርገዋል። ለሉሲ አፋር ቤቷ ነው፤ ሀዳር የተባለው ስፍራ ደግሞ መገኛዋ ነው። በመሆኑም በዚህ ከሰው ልጅ መገኛ ጋር የተቆራኘን ስፍራ ሙዚየም ገንብቶ፣ የቱሪስት መስህብ አልምቶና አካባቢውን በስፋት አስተዋውቆ የገቢ ምንጭ ማድረግ ሲቻል ለምን ተዘንግቶ ቆየ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ይሆናል። የጊዜ ጉዳይ ሆኖ አሁን አፋር ሰመራ ላይ በሉሲ የተሰየመ የሀገር ታሪክና ቅርስ ማጣቀሻ፤ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ማሳያ የሆነ ሙዚየም ለመገንባት ዝግጅት መደረጉ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል።   የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር)፤ የሚገነባው ሙዚየም የሀገር ታሪክና ቅርስ የሚሰነድበት፣ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ተጠብቀው የሚዘልቁበት፣ የሰው ልጅ አመጣጥና ዝግመተ ለውጥ የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ የሚካሄድበት ይሆናል ብለዋል። እሳቸው እንዳሉት የሙዚየሙ ግንባታ በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገለግሎት የሚበቃ ይሆናል። የአፋር ክልል በመስኖ ቢያለሙበት፣ የጥጥ እና የቴምር ልማት ቢካሄድበት ተዝቆ የማያልቅ እምቅ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በለውጡ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን እምቅ የቱሪዝም ሃብቱንም በማልማትና በመጠበቅ የሃገር ሃብት የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የሉሲ ሙዚየም ግንባታ ሁነኛ ማሳያ ነው። የሳምንቱ ቅኝታችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ በቀጥታ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝተናል። አሶሳ በሳምንቱ በሃይማኖት አባቶች ጸሎትና ዱአ ተባርካ ስለ ሰላምና አብሮነት የሚመከርባት ከተማ ሆና እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። የተለያዩ የኃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት 7ኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ "ሰላምን ይበልጥ ለማስፋት እና ለማስረጽ የሃይማኖቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ አባቶች ስለ ሰላም እና አብሮነት እንትጋ ለትውልድ ግንባታም መስራት ግድ ይለናል በማለት አፅንኦት በመስጠት መክረዋል።   የኢትዮጵያ ሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኃይማኖቶች ለሰላም እና ለህዝቦች አብሮነት ያላቸውን አስተምህሮ በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ እና ሀገራዊ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን አለባቸው ብለዋል። በኢትዮጵያ ሰላምን ለማጽናት እና የወንድማማችነት ድልድይን ለመገንባት እንስራ በማለትም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ስንጓዝ የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ-AGRA) ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የኤልቶ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ዩኒየን የሥራ እንቅስቃሴን መጎብኘታቸውን እናገኛለን። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጥምረቱ የቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ አርሶ አደሮች ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ጥሩ ተስፋ የተሰነቀበት መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። የግብርና ልማትን የማዘመን፣ ምርታማነትን የማሳደግና የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል።   የጥምረቱ ፕሬዚዳንት አሊስ ሩህዌዛ፤ በአፍሪካ የግብርና ስርዓት ሽግግርን ለማጠናከር በተለይም አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። በአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ሂደት ውስጥ ደግሞ የኢትዮጵያ ለውጥ አስደናቂ ስለመሆኑ አንስተዋል። ሌሎች በዚህ ሳምንት በሁሉም ክልሎች ባደረግነው ምልክታ በተለይም የምርጫ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኖ ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን እየወሰዱ ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎችም የምረጡኝ ቅስቃሳ ማድርጋቸውን ቀጥለዋል። የግብርና ልማት ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እና ሌሎችም የልማት ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ የቀጠሉበት ሳምንት ነበር ማለት ይቻላል።
የጤና ነገር …
Apr 17, 2026 281
በዮሐንስ ደርበው ማዲያት ታክሞ ይድናል? እነማንንስ ያጠቃል? የሥነ-ውበት ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ሱመያ ኑርሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለማዲያት መንስዔ፣ ምልክቶች እና ሕክምና ሙያዊ ሐሳባቸውን አጋርተዋል። እንደ ባለሙያ ቢደረግ ያሉትንም መክረዋል። • ማዲያት እነማንን ያጠቃል? ማዲያት ማንኛውንም ሰው እንደሚያጠቃ ያነሱት ዶ/ር ሱመያ፤ በብዛት ግን በሴቶች ላይ እንደሚከሰት ያስረዳሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ እርግዝና ላይ ያሉ እንዲሁም የወሊድ መከላከያ የሚወስዱ ሴቶች እና ሆርሞናል ቴራፒ ላይ ያሉ ሰዎች በስፋት ለማዲያት ተጋላጭ ናቸው። በተጨማሪም በብዛት ምግብ ማብሰል (ኪችን) ላይ የሚሠሩ ሰዎች ለማዲያት እንደሚጋለጡ ጠቁመዋል። ባብዛኛው ማዲያት የሚያጠቃው በዕድሜ ከ25 ወይም ከ30ዎቹ በላይ የሆኑትን መሆኑንም አንስተዋል። • መንስዔ እንደ ዶክተር ሱመያ ገለጻ፤ ለማዲያት ከሚያጋልጡ መንስዔዎች መካከል ዋነኛው የፀሐይ ጨረር ነው። በተጨማሪም ሆርሞናል ፋክተር (የወሊድ መከላከያ መጠቀም፣ እርግዝና ላይ መሆን፣ ሆርሞናል ቴራፒ መውሰድ) ለማዲያት አጋላጭ መንስዔ ሆነው ይጠቀሳሉ ይላሉ። ጭንቀት እንዲሁም ቆዳን የሚያስቆጡ ነገሮች ለማዲያት አጋላጭ መሆናቸውንም ነው ያብራሩት። • ምልክቶች ማዲያት ቀላ፣ ጠቆር ወይም ደብዘዝ ያለ ቀለም (መልክ) ይዞ ከትንሽ ጀምሮ የሚሰፋ መሆኑን ዶክተር ሱመያ አስገንዝበዋል። ለምሳሌ ይላሉ፤ ጉንጭ ላይ መውጣት ቢጀምር ወደ ሁለቱም ጉንጮች ከዚያም ወደ ግንባር እንዲሁም አገጭ እና አፍንጫ ሊደርስ እንደሚችል ገልጸዋል። በሂደትም የማቃጠል፣ የመቆጥቆጥ እና ማሳከክ ሁኔታ ሊኖረው እንደሚችል ነው ያነሱት። • ሕክምና መንስዔዎቹን ዐውቆ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ያስገነዘቡት ዶክተር ሱመያ፤ የፀሐይ ጨረር መከላከያዎችን መጠቀም፣ በሕክምና የሚሰጡ መድኃኒቶችን ሳያቋርጡ በትዕግስት መጨረስ (ቶሎ ለውጥ አላየሁበትም ብሎ አለማቋረጥ) እንደሚገባም መክረዋል። የማዲያት ሕክምና ስኬታማነቱ ለሁሉም ሰው በዕኩል ጊዜ እንደማይታይ በመግለጽ፤ እንደተከሰተበት ጊዜ ከሰው ሰው እንደሚለያይ በአጽኦት ተናግረዋል። ለምሳሌ አሉ፤ ዓመታት ያለፉት ማዲያት እና 2 ወራት የሆኑት ሕክምና እኩል ቢጀመርም በተመሳሳይ ጊዜ ላይድኑ እንደሚችሉ አመላክተዋል። ስለዚህ የሌላኛው ድኖ የኔ አልዳነም በሚል ሕክምናን ማቋረጥ ስህተት መሆኑንም ነው ያስረዱት። በሌላ በኩል ማዲያትን አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠው፤ ይህም የሚሆነው መንስዔዎቹን በማወቅ የማዲያት ተጋላጭ ባለመሆን ነው ብለዋል። ከተቻለ በየሥድስት ወሩ ወይም በየዓመቱ የቆዳ ጤና ምርመራ ማድረግ እና ያለበትን ደረጃ ማወቅም የሚከሰት ችግር ቢኖር እንኳ ሥር ሳይሰድድ በማከም ቶሎ እንዲድን ማድረግ ይቻላል ነው ያሉት።
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 13, 2026 215
በምግብ ራስን የመቻል ጉዞ አንዱ ምሰሶ - የስንዴ ልማት በሙሴ መለሰ ስንዴ በኢትዮጵያ በከፍትኛ ደረጀ ከሚመረቱና ለግብይት ከሚውሉ የሰብል ምርቶች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የስንዴ አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል በግንባር ቀደምነት ትጠቀሳለች። ከ2011/2012 የምርት ዘመን በፊት ኢትዮጵያ በመኸር የምታለማው ስንዴ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን ሔክታር ያልበለጠ ነበር። የበጋ መስኖ ስንዴ ሲጀመርም 3 ሺህ ሔክታር ብቻ እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በመኸር፣ በበጋ መስኖ እና በበልግ ወቅት 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ እያለማች እንደምትገኝ የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያስረዳል። ሚኒስቴሩ የ2018 ዓ.ም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ 4 ነጥብ 29 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ በማልማት ከበጋ መስኖ ስንዴ 175 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን መግለጹ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በአብዛኛው የስንዴ ምርት የሚመረተው በአነስተኛ አርሶ አደሮች ነው። ባለፉት ዓመታት ግን የሜካናይዝድ እርሻ የስንዴ ምርቱን በእጥፍ እንደጨመረው ይገለጻል። መንግሥት መስኖን በመጠቀም ስንዴን በዓመት አንድ ጊዜ ከማምረት ወደ ሦስት ጊዜ ማምረት የሚቻልበትን አሰራር በመፍጠር የሀገሪቱን ምርታማነት ለማሳደግ እየሠራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ107 ሚሊየን ኩንታል በላይ ነው። ይህንን ፍላጎቷን ለመሙላት ለዓመታት ከ700 ሚሊየን ዶላር እስከ 1 ቢሊየን ዶላር ለስንዴ ግዥ ወጪ ታደርግ ነበር። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ትሸፍን የነበረውም ከውጭ በምትገዛው ስንዴ ነበር። መንግሥት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በማስፋፋትና በየዓመቱ የሚመረትበትን ዙር በመጨመር ኢትዮጵያ የስንዴ ፍጆታዋን ሙሉ በሙሉ እንድትሸፍን በትኩረት ሲሠራ ቆይቷል። በዚሁ በ2014 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገር ስንዴ ማስገባት አቆመች። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያገኘችው ውጤት ከውጭ ማስገባትን ማስቆም ብቻ አልነበረም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ራስን ብቻ ሳይሆን ኤክስፖርት የማድረግ ዐቅም እንዳላት በመግለጽ፤ ስንዴ ወደ ውጪ መላክ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስቀመጡት ሀገራዊ ግብ መሰረት ኢትዮጵያ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ውጭ የመላክ ተግባርን በይፋ አስጀምራለች። የስንዴ ኤክስፖርቱ ኢትዮጵያ ገጽታዋን የሚለውጥ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ መግባቷን የሚያመላክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ገልጸው ነበር። ኢትዮጵያ በ2015 ዓ.ም የሀገር ውስጥ ፍጆታዋን ሸፍና 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ የማቅረብ ዐቅም እንዳላት ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚና የኤክስፖርት ኮሚቴ አረጋግጧል። ኮሚቴው የሀገራዊ የነፍስ ወከፍ ፍጆታና የሀገሪቱን አጠቃላይ የምርት ሚዛን በማጥናት ከፍጆታ የሚተርፍ 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ወደ ውጭ መላክ እንደሚቻልም ተገልጿል። 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ባሳለፍነው የካቲት ወር በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄዱ የሚታወስ ነው። በወቅቱም የአፍሪካ ሕብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ከጉባዔው ጎን ለጎን በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ ተምሳሌታዊ የሆነ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስንዴ ምርታማነቷን በማሳደግ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን ባለፈ ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሏን ሕብረቱ መመልከት መቻሉንም ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት በዓመት ውስጥ ለምግብ ምርቶች ከሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ ስንዴ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከውጭ የሚገባውን ምርት በሀገር ውስጥ ስንዴ መተካት እንደሚቻል በተግባር ያሳየችበት መንገድ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን ተሞክሮ ወስደው ወደ ተግባር እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ሥራ ላይ እያሳየች ያለውን ሥራ አስፍታ ከቀጠለች በምግብ ራሷን የመቻል ሕልሟን የማሳካት እድሏ ሰፊ መሆኑንም ማመላከታቸው ይታወሳል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 932
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ ‎በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ‎ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
የንፋስ ኃይል፤ የኢትዮጵያ የብርሃን አድማስ የአረንጓዴ ልማት ሌላኛው ብስራት!!
Apr 18, 2026 139
በቁምልኝ አያሌው የሰው ልጅ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን መጠቀም የጀመረው በጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዘመን እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። ለአብነትም፤ ግብፃውያን ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት ጀልባዎችን በባሕር ላይ ለመንዳት የንፋስ ኃይልን ይጠቀሙ ነበር። በሰባተኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ደግሞ ፋርስ (የአሁኗ ኢራን) የመጀመሪያውን በንፋስ ኃይል የሚሠራ የጥራጥሬ መፍጫ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ ማዋል ጀመረች። ግሪኮችና ሮማውያን የውሃ መንኮራኩሮችን በመጠቀም እህል መፍጨት የሚያስችል ፈጠራን እንዳስጀመሩ የታዳሽ ኃይል የታሪክ ማኅደሮች ይጠቁማሉ። ጥንታዊያን ሕዝቦች የፀሐይ ኃይልን ለብርሃንና ለሙቀት ምንጭነት ከመጠቀም ባለፈ፣ የፀሐይ ጨረርን በማሰባሰብ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚጠቀሙባቸውን ጥበቦች ነበሯቸው። ምንም እንኳን የ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢንዱስትሪ አብዮት በድንጋይ ከሰልና በተፈጥሮ ዘይት የበላይነት ቢያዝም፤ በዚሁ ወቅት ለታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ልማት መሠረት መጣሉን ታሪክ ያስትውሰናል። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው እ.አ.አ በ1839 ፈረንሳዊ የፊዚክስ ሊቅ ኤድመንድ ቤኩረል፤ የፀሐይ ብርሃንን ወደ ኤሌክትሪክ መቀየር የሚቻልበትን የ'ፎቶቮልታይክ' (Photovoltaic effect) ክስተት ማገኘቱ ነው። በተጨማሪም እ.አ.አ በ1882 የመጀመሪያው በውሃ ኃይል የሚሰራ የኤሌክትሪክ ማመንጫ በአሜሪካ ሥራ ጀመረ። እ.አ.አ በ1883 ደግሞ በኦስትሪያ ቪየና በተካሄደው ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ኤግዚቢሽን፣ የንፋስ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ የሚቀይሩ ተርባይኖችን ለመትከል የሚያስችሉ ወሳኝ የቴክኖሎጂ ዕድሎች ታይተዋል። በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ለታዳሽ ኃይል የሚሰጠው ትኩረት መቀዛቀዝ ቢያሳይም፣ በ1970ዎቹ የተከሰተው ዓለም አቀፍ የነዳጅ እጥረት ዓለም አማራጮችን እንድታማትር አስገድዷታል። በዚህም ምክንያት የነዳጅ ዋጋ መናር ሀገራት ከነዳጅ ጥገኝነት ለመውጣት ወደ ውሃ፣ ፀሐይና ንፋስ ኃይል ፊታቸውን እንዲያዞሩና በዘርፉ ለሚካሄድ ጥናትና ምርምር ከፍተኛ መነሳሳት እንዲፈጠር አድርጓል። የንፋስ ኃይል ታሪካዊ ዳራና የቴክኖሎጂ እድገት የንፋስ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ የመቀየር ታሪክ እ.አ.አ በ1883 በኦስትሪያ ቪየና በተካሄደው ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ኤግዚቢሽን ላይ ፍሬድላንድ በተሰኙ ሳይንቲስት አማካኝነት የመጀመሪያው የንፋስ ኤሌክትሪክ ተርባይን ለእይታ መቅረቡ ይነገራል። ይህ የፈጠራ ሥራ በየጊዜው እየተሻሻለ መጥቷል። በ1887 ስኮትላንዳዊው የኮሌጅ ፕሮፌሰር ጄምስ ብሊዝ የቤታቸውን መብራት ለማብራት የተጠቀሙበት የንፋስ ተርባይን በዘርፉ ትልቅ እመርታ ተደርጎ ይወሰዳል። ፕሮፌሰሩ ቀስ በቀስ የፈጠራ ውጤታቸውን አሳድገዋል። የአካባቢው ማኅበረሰብም የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ እንዲሆን ያቸሉትን አድርገዋል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታ በበርካታ ሀገራት የተለያዩ ሙከራዎች መደረጉን ድርሳናት ሲፈተሹ የሚያሳዩት እውነት ነው። ሆኖም ዘርፉ ትኩረት አግኝቶ እንዲያድግ ያደረገው በ1973 በዓለም ላይ የተከሰተው የነዳጅ ቀውስ ነው። ይህ ክስተት ሀገራት ወደ አማራጭ ኃይል ምንጮች እንዲያተኩሩ ዕድል ፈጥሮላቸዋል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ መጠነ ሰፊ የንፋስ ኃይል እርሻዎችን (Wind Farms) በመገንባት ግንባር ቀደም መሆን ችላለች። እ.አ.አ እስከ 2008 ድረስ ከዘርፉ የምታመነጨውን የኃይል መጠን ወደ 24.4 ጊጋ ዋት አሳድጋለች። የንፋስ ኃይል የማመንጨት ሂደት የንፋስን የተፈጥሮ እንቅስቃሴ በተርባይኖች አማካኝነት ወደ ሜካኒካዊ ኃይል፣ በመቀጠልም ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚቀይር ዘመናዊ የታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ነው። ሂደቱም የተርባይን ክንፎች በንፋስ ግፊት አማካኝነት በሚፈጥሩት ሽክርክሪት ጀኔሬተሩን በማንቀሳቀስ ኤሌክትሪክ እንዲመነጭ ያደርጋል። የዓለማችን ግዙፍ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች የት ይገኛሉ? በአሁኑ ወቅት በዓለማችን ከ350 ሺህ በላይ የንፋስ ተርባይኖች ተተክለው ኃይል እየሰጡ ይገኛል። ቻይና በንፋስ ኃይል ማመንጨት የዓለማችን ቀዳሚ ሀገር ስትሆን፤ አሜሪካ እና ጀርመን በቅደም ተከተል ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። የቻይናው ጂኳን (Gansu) የንፋስ ኃይል ማመንጫም ከ20,000 ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ያለ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው። የንፋስ ኃይል በኢትዮጵያ ዓለም ለታዳሽ ኃይል ልማት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ የንፋስ ኃይል ልማት ቀዳሚ ተዋናይ የሚያደርጋትን ስራዎች እያከናወነች ነው። ሀገሪቷ በምስራቅ አፍሪካ ያላት ስትራቴጂካዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ የታደለችውን የተፈጥሮ ፀጋ ወደ አማራጭ ኃይል ለመቀየር ሰፊ ዕድል ፈጥሮላታል። በንፋስ ኃይል ልማት የመጣው ከፍተኛ ለውጥም የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፍላጎትን በመሙላት የብዝኅ ታዳሽ ኃይል አማራጭ ልማት እንዲጎለብት እያደረገ ይገኛል። የተፈጥሮ ስጦታና ያልተነካው የኢትዮጵያ እምቅ የንፋስ ኃይል ፀጋ ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አኳያ በንፋስ ኃይል አማራጭ እምቅ የመልማት ፀጋን ተችሯታል። በተለይም የታላቁ ስምጥ ሸለቆ፣ ሰሜናዊ ተራራማ ስፍራዎችና ምስራቃዊ ቆላማ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የንፋስ ፍጥነት ኃይልን ለማመንጨት ተስማሚ መልክዓ ምድሮች ናቸው። በዚህም ኢትዮጵያ እስከ አንድ ነጥብ ሦስት ሚሊዮን ሜጋ ዋት የንፋስ ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይህ አሃዛዊ መረጃም ከአሁኑ ወቅት አጠቃላይ ኃይል የማመንጨት አቅም ጋር ሲነፃጸር ሰፊ የልማት ዕድል መኖሩን ያረጋግጣል። ከጅምር እስከ ዛሬ የስኬት ጉዞ ምዕራፍ የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት በ2001 ዓ.ም አሸጎዳ ፕሮጀክት ግንባታ ተጀምሯል። በአዳማ 1 እና 2 ስራውን በማስፋት አሁን ላይ እስከ አይሻ 1 እና አሰላ ፕሮጀክቶች ደርሷል። እነዚህ የአዳማ፣ የአሸጎዳ፣ የአይሻ እና የአሰላ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል አድማስ መስፋፋትን የሚያረጋግጡ ናቸው። ለሀገሪቷ አረንጓዴ ልማት ብስራት የሆኑ ታላላቅ ስራዎች ናቸው። አዳማ-1 እና ሁለት፡- በአጠቃላይ 204 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው የአዳማ የኤሌከትሪክ ማመንጫዎች የኢትዮጵያን የንፋስ ኃይል የማመንጨት አቅም በተግባር ያረጋገጡ ፋና ወጊዎች ናቸው። አሸጎዳ፡- በፈረንሳይ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ የተገነባ ሁለተኛው የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ነው። 120 ሜጋ ዋት የሚያመነጨው ይህ ጣቢያ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሚገኙ ዜጎች ከሚሰጠው ብርሃን በተጨማሪ የኢንዱስትሪ አቅም ሆኗል። አይሻ-2፡- በቅርቡ ተመርቆ ወደ ስራ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 80 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል። በኢትዮ-ጅቡቲ ድንበር አቅራቢያ መገናባቱም ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው። አሰላ፡- በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን የምትገኝ የኢትዮጵያ ብርቅየ አትሌቶች መፍለቂያ ስፍራ ናት። በስንዴና ገብስ የግብርና ምርታማነትም በተምሳሌትነት ትጠቀሳለች። ነፋሻማ የአየር ሁኔታዋም ለኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አቅም የሚሆን ፀጋን ተችሯታል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ 08 ቀን 2018 ዓ.ም 100 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚያስችለውን የአሰላ ንፋስ ኃይል መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም አርሲ በስንዴና ገብስ ብቻ ሳይሆን በንፋስ ኃይልም የኢትዮጵያ ብልፅግና ማዕከል መሆኗን የአካባቢውን የብዝኅ ፀጋ አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም ኢትዮጵያ ከዕዳና ኪሳራ ወጥታ ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜ ማጠናቀቅና ማትረፍ መጀመሯን በተግባር ያሳየ ነው። ከዚህም በላይ በንፋስ እና በጂኦተርማል ኃይል ማመንጫዎች የኢነርጂ ማዕከል እየሆነ መምጣቷን ያረጋግጣል። "አርሲ በኃይል ዘርፍ ልክ እንደ ስንዴ እና ገብስ ተጨማሪ አቅም ያለው አካባቢ መሆኑን ማየት ችለናል" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በንግግራቸው። የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ በ145 ሚሊዮን ዩሮ ወጪ የተገነባ መሆኑን በመጥቀስ፤ ፕሮጀክቱ በአዋጭነት ደረጃ ሲታይ እጅግ ስኬታማ ነው ብለዋል። ከዚህ ቀደም የሚወሰዱ ብድሮች ለትውልድ ዕዳ ትተው የሚያልፉ እንደነበሩ በማስታወስ፣ የአሁኑን ፕሮጀክት የተለየ የሚያደርገውን ነጥብ ሲያነሱ ይህ ፕሮጀክት ቢበዛ በሁለት ዓመት ሙሉ ወጪውን ሸፍኖ ትርፋማ ስለሚሆን ልጆቻችን ትርፍ ሀብት የሚያገኙ እንጂ ዕዳ የሚረከቡ አይሆኑም በማለት ነው የገለጹት። ፕሮጀክቱ እውን እንዲሆን ግማሹን በእርዳታ እንዲሁም ቀሪውን ከወለድ ነጻ በሆነ ብድር ላቀረበችው የዴንማርክ መንግሥት የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱም ቢበዛ በሁለት ዓመት ሙሉ ወጪውን ሸፍኖ ትርፋማ ስለሚሆን ልጆቻችን ምንዳ እንጂ ዕዳ የሚረከቡ እንደማይሆን አስገንዝበዋል። በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ ላይ በደማቅ ሁኔታ የተመረቀው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት የጀመረችውን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ሌላኛው ታሪካዊ አሻራ ነው። በመደመር መንግስት መፅሐፍ ገፅ 206 ላይ እንደተጠቀሰው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋት ባለፉት ዓመታት ሰፊ ኢንቨስትመንት ተካሂዷል። ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትም ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷል። የታላቁ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫን ጨምሮ ሌሎች በጅምር ያሉና በሚገባ አገልግሎት እየሰጡ ያልነበሩ ማመንጫዎችን ወደ መስመር ለማስገባት ተችሏል። በዚህም ሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚያስፈልጋትን የኃይል አቅርቦት በሚገባ መሸፈን ችለናል በማለት ተከትቧል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 504 ሜጋ ዋት ኃይል ብሔራዊ የኃይል ቋትን በመመገብ የኃይል አቅርቦት የጀርባ አጥንት ሆነዋል። በኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ቀደም ሲል የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በመንግስት ብቸኛ ይዞታነት ብቻ ሲካናወኑ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት ግን ይህን አሰራር የሚቀይር የፖሊሲ ማሻሻያ ተደርጓል። ባለሃብቶች በመንግስትና የግል አጋርነት (PPP) ማዕቀፍ የሚሳተፉበት ሰፊ ዕድል ለመፍጠር ተችሏል። ይህም የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ከማበረታታቱም በላይ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የግሉን ዘርፍ በኃይል ልማት ላይ ለማሳተፍ የተወሰዱት የፖሊሲ እርምጃዎች አሁን ላይ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ጀምረዋል። ለአብነትም፤ በሶማሌ ክልል በመንግስትና በግል አጋርነት የሚገነባው የአይሻ-1 እና 3 የንፋስ ኃይል ፕሮጀክት ከ300 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን ባለፈ፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለውን የኃይል ትስስር በማጠናከር ለጋራ ዕድገት መፋጠን ጉልህ ፋይዳ አለው። ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ በመገንባትና የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቀነስ ረገድ የምትከተለው የልማት መንገድ ለሌሎች ሀገራትም ተምሳሌት የሚሆን ነው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ከብርሃን ባሻገር የንፋስ ኃይል የኢትዮጵያን የኃይል አቅርቦት በማሟላት ለሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ስትራቴጂክ መሰረት እየጣለ ይገኛል። ለአብነትም በኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ እያበረከተ ያለውን ፋይዳ መጥቀስ ይቻላል። የኢነርጂ ዋስትና እና የኃይል ምንጭ ስብጥር፡- በኢትዮጵያ ከውሃ ኃይል የማመንጨት ተግባር ቀዳሚውን ድርሻ ይይዛል። ይህም በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በሚከሰት የድርቅ አደጋ የኃይል አቅርቦት ተጋላጭነት በማስፋት ተፅዕኖ ያሳድራል። የንፋስ ኃይልም የአቅርቦት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ጉልህ ስትራቴጂክ ፋይዳ አለው። በበጋ ወራት የውሃ መጠን ሲቀንስ የንፋስ ኃይልን በመጠቀም ደግሞ የተፈጥሮ ሚዛንን የጠበቀ አስተማማኝ የኃይል ስብጥር ለመገንባት ጉልህ ፋይዳ ያበረክታል። የኢንዱስትሪ መፋጠንና የሥራ ዕድል፡- የኃይል አቅርቦት ለአስተማማኝ የኢንዱስትሪ ምርታማነት የጀርባ አጥንት ነው። የኢንዱስትሪው ዘርፍ ደግሞ ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ሚና አለው። በተለይም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገነቡ የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶች የዕውቀትና የምርታማነት ሽግግርን በማፋጠን ረገድ ፋይዳቸው የጎላ ነው። እነዚህ ፕሮጀክቶች በንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ተከላና ጥገና ወቅት የዜጎችን የምህንድስና ክህሎት በማጎልበት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግሩን በተጨባጭ ያጠናክራሉ። ፋብሪካዎች አስተማማኝ ኃይል እንዲያገኙ በማድረግ የገቢ ምርቶችን የመተካትና የወጪ ንግድ አቅማቸውን በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ። ቀጣናዊ ትስስርና የውጭ ምንዛሬ ግኝት፡- የኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከልነት አቅም የሚያጎለብቱ ከአነስተኛ እስከ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል፤ በመገንባታ ሂደትም ናቸው። የንፋስ ኃይል ልማትም ቀጣናው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን እየደገፈ ይገኛል። ይህም የዕድገት ትስስርን በማፋጠን በየዓመቱ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያበረክታል። የአረንጓዴ አሻራና የአካባቢ ጥበቃ፡- የንፋስ ኃይል ከብክለት የፀዳ ንፁህ የኃይል ምንጭ ነው። ይህም ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት የተቸራትን ዓለም አቀፍ ዕውቅና ለማፅናት በቀላሉ አይታይም። የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ የፋይናንስ ገቢን በማሳደግም ተጨማሪ የታዳሽ ኃይል ልማትን ለማጠናከር ያስቻላል። የገጠሩን ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚነት በማስፋትም የአካባቢና የደን መራቆትን ለመቀነስ ያስቻል። የንፋስ ኃይል ልማት ለኢትዮጵያ ቅንጦት አይደለም፤ ይልቁንስ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ዕድገትን የማፋጠን የህልውና ጉዳይ ነው። ለዚህም የንፋስ ኃይል ፀጋዎችን በማልማት ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የንፁህ ኢኮኖሚ ግንባታ ፋና ወጊነት የሚያረጋግጥ የልማት አቅጣጫ ተተልሞ እየተሰራበት ነው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማትም አዲስ ተስፋን የፈነጠቀ የብርሃን አድማስና የአረንጓዴ ልማት ሌላኛው ብስራት እየሆነ ይገኛል።  
በፈተናዎች ሁሉ የጸናው የኢትዮጵያና የላይቤሪያ ወዳጅነት
Apr 14, 2026 1176
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያና ላይቤሪያ ዘመናትን የተሻገረ ወዳጅነት አላቸው። ይሄ ወዳጅነት በፈተናዎች ጊዜ ሁሉ ጸንቶ የዘለቀም ነው። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ውስጥ ብቸኛ ነፃ ሀገራት በመሆናቸው፣ በዓለም አቀፍ መድረኮች (ለምሳሌ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ) የአፍሪካውያን ድምፅ ሆነው በጋራ ይቆሙም ነበር። የሀገራቱ የወዳጅነት እና የትብብር ስምምነትም እ.አ.አ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ የጀመረ ሲሆን፣ በመካከላቸው ያለው ዘላቂ ወዳጅነት እና በዓለም አቀፍ መድረኮች (እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት) በጋራ ለመቆም ቃል የተገባበት ሰነድም ተደርጎ ይወሰዳል። የዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሠረት የጣሉትም ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እና ፕሬዝዳንት ዊሊያም ቱብማን ናቸው። እ.ኤ.አ. በ1954 ፕሬዝዳንት ቱብማን ወደ አዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ይፋዊ ግንኙነት እንዲጀመር በር ከፍቷል። ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እ.አ.አ. 1958 ጉብኝት ወደ ሞንሮቪያ በማድረግ፣ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኙ የነፃነት ንቅናቄዎችን በጋራ ለመደገፍ ተወያይተዋል። እነዚህ ጉብኝቶች የሁለትዮሽ ብቻ ሳይሆኑ አህጉራዊ ፋይዳም ነበራቸው። እ.አ.አ በ1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ሲመሰረት፣ ሁለቱ ሀገራት "የሞንሮቪያ" እና "የካዛብላንካ" ቡድኖችን ልዩነት በውይይት በመፍታት ለአህጉሪቱ አንድነት የጀርባ አጥንት መሆናቸውን አስመስክረዋል። በ1960ዎቹ መጀመሪያ ላይ በ”ሞንሮቪያ ቡድን” እና "የካዛብላንካ ቡድን" መካከል የነበረውን ልዩነት ለማጥበብ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በጋራ በመስራታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሊመሰረት ችሏል። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በችግር ውስጥ የተፈተነ ወዳጅነት ነው የሚል ሀሳብ በብዙዎች ይነሳል። የዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ በላይቤሪያ የነበራት የሰላም ማስከበር ሚና ነው። ላይቤሪያ ለ14 ዓመታት በዘለቀው አውዳሚ የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት መንግሥታዊ መዋቅሯ ፈርሶ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2003 የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ሰላም እንዲያስከብሩ ከጠራቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ ነበረች። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ በርካታ ሰራዊቷን በማሰማራት ለሀገሪቷ ሰላም ዋጋ ከፍላለች። ሰራዊቱ አማፂያንን ትጥቅ በማስፈታት፣ ተዋጊዎች ከማህበረሰብ ጋር እንዲቀላቀሉ በማድረግ እና የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ከፍተኛ ስራ ሰርቷል። ዋና ከተማዋ ሞንሮቪያ እና በገጠራማ አካባቢዎች የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንዳይጣስ ጥብቅ ቁጥጥር አድርጓል። የኢትዮጵያ ሰራዊት የጤና ቡድን በየሰፈሩ በመዘዋወር ለላይቤሪያውያን ነፃ የህክምና እርዳታ እና መድሃኒትም ይሰጥ ነበር። ሰራዊቱ የራሱን ስንቅ ለተቸሩ ዜጎች በማካፈል ወንድማማችነትን በተግባር አሳይቷል። እ.ኤ.አ በ2014 የኢቦላ ወረርሽኝ በላይቤሪያ በከፋ ሁኔታ በተከሰተበት ወቅትም፣ ሌሎች ሀገራት ሰራዊታቸውን ሲያስወጡ ኢትዮጵያ ግን የህክምና ቡድኖችን እና ሰራዊቷን በማቆየት ከላይቤሪያ ህዝብ ጎን ቆማች። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ ሶስት ተከታታይ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫዎች እንዲካሄዱ በሰላም ማስከበሩ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የላይቤሪያ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች የላቀ አገልግሎት ሜዳሊያ እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ የነበራት የሰላም ማስከበር ሚና ከወታደራዊ ተልዕኮ ባለፈ የደም እና የአጥንት መስዋዕትነት ከፍላለች። ይህ የሰራዊቱ ተሳትፎ ዛሬም ድረስ በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ላለው ጥብቅ ወዳጅነት ዋነኛው ምክንያት ተደርጎ ይወሳል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራቱ መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች ለሁለትዮሽ ትብብሩ መጠናከር አስተዋጽኦ አድርገዋል። የቀድሞዋ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ እ.አ.አ በ2006 ስልጣን በያዙ ማግስት አዲስ አበባን ጎብኝተዋል። ይህም ኢትዮጵያ በላይቤሪያ ሰላም ለማስፈን ላደረገችው ድጋፍ እውቅና የሰጡበት ነበር። ሰርሊፍ በላይቤሪያ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ሲያበቃ እ.አ.አ ጁላይ 2015 ኢትዮጵያን በመጎብኘት ለተደረገላቸው የህክምና ቡድን ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። የቀድሞዋ ፕሬዝዳንት እ.አ.አ በ2017 ለሶስት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳላኝ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ፕሬዝዳንቷ በወቅቱ የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክን የጎበኙ ሲሆን ላይቤሪያ ከኢትዮጵያ የጨርቃ ጨርቅ ልማት ዘርፍ ልምድ መቅሰም እንደምትፈልግ በወቅቱ ገልጸው ነበር። የላይቤሪያ የእግር ኳስ ኮከብ እና የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ እ.አ.አ በ2018 ስልጣን ከያዙ በኋላ በአዲስ አበባ በተካሄደው 30ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የተሳተፉ ሲሆን ከጉባኤው ጎን ለጎን ከወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ተገናኝተው በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ተወያይተዋል። የቀድሞው የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲ-ማክስዌል ሳህ ከማያህ እ.አ.አ በ2022 በአዲስ አበባ ጉብኝት በማድረግ በሁለቱ ሀገራት መካከል የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን (Joint Ministerial Commission) እንዲቋቋም ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በላይቤሪያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (UNMIL) ላይ በነበረበት ወቅት፣ የተለያዩ የመከላከያ ሚኒስትሮች እና የጦር አዛዦች የኢትዮጵያን ሰላም አስከባሪ ኃይል ለመጎብኘት እና ከላይቤሪያ ባለስልጣናት ጋር ለመወያየት በተደጋጋሚ ወደ ሞንሮቪያ ተጉዘዋል። ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ውይይቶች በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነቶችም ተፈራርመዋል። ሰላም ፣ ደህንነት፣ ጤና፣ የአየር አገልግሎት፣ የቪዛ ነፃ መብት ፣ የንግድ ትብብር ማዕቀፍ፣ ግብርና፣ ትምህርት፣ ባህል እና ስፖርት ስምምነት ከተደረገባቸው ዘርፎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአየር አገልግሎት ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞንሮቪያ ያለምንም ገደብ እንዲበር እና ላይቤሪያን ከቀሪው ዓለም ጋር ማገናኘት የሚያስችል ህጋዊ ማዕቀፍ ነው። የሰላም ማስከበር ስምምነቱ በተባበሩት መንግሥታት ማዕቀፍ ውስጥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል እንድትልክ የተደረገው ስምምነት በላይቤሪያ መረጋጋት እንዲመጣ ትልቅ ድርሻ ነበረው። በኪነ-ጥበብ እና በስፖርት ዘርፍ (በተለይም በእግር ኳስ) የሁለቱ ሀገራት ወጣቶች ልምድ እንዲለዋወጡ የሚያስችሉ የመግባቢያ ሰነዶች ተፈርመዋል። የወቅቱ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦአከይ እ.አ.አ 2023 ፕሬዝዳንት ሆነው በተመረጡበት ወቅት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ለማደስ እና በንግድ ዘርፍ በጋራ ለመስራት ፍላጎታቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም ከተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ከላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦአካይ ጋር ውይይት አድርገዋል። የሁለትዮሽ ውይይቱ በቴክኖሎጂ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ኢትዮጵያ ለመገንባት ባቀደችው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ላይ ያተኮረ ነበር። በውይይቶቹ ላይ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በንግድ እና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። የላይቤሪያው ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ለስራ ጉብኝት ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክትም የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የነገ ብሩህ ተስፋ እየተሰራባት ወደ ምትገኘው ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ እንኳን በሰላም መጡ ብለዋል። በፕሬዝዳንቱ ቆይታ እጅግ ፍሬያማ ውይይት እንደሚኖራቸውም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። የፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የስራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ወዳጅነት የበለጠ እንደሚያጠናክርም ታምኖበታል። የኢትዮጵያ እና የላይቤሪያ መጻኢ ግንኙነት ከታሪካዊ ወዳጅነት ወደ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ አጋርነት የማሳደግ ፍላጎት በሁለቱም ወገን በኩል አለ። በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የአቪዬሽን ትስስር፣ የቴክኖሎጂ ልውውጥ እና በአህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጠና (AfCFTA) ማዕቀፍ የሚደረግ ትብብር ለጋራ ብልጽግና መሰረት ይጥላል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 11, 2026 193
ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ • ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ የትንሣኤ በዓል በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በዓል ነው፤ ሞት የተሻረበትና ሕይወት ዋስትና ያገኘበት ነው ብለዋል። የትንሣኤ በዓል ከሞት ባሻገር ሕይወት ከመቃብር ባሻገር ትንሣኤ መኖሩ የታወጀበት መሆኑንም ገልፀው፤ ሞት መጨረሻ መቃብር መዳረሻ አለመሆናቸው የተረጋገጠበት ነው ብለዋል በመልዕክታቸው። የዘንድሮውን ትንሣኤ የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በሚያልፍ ፈተና ውስጥ እንዳለች እያሰብን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን ሲሉ ገልፀዋል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ በጥልቁ ጨለማ ጠፍተን እንድንቀር አሥረው ለመያዝ የሚሞክሩ ወጥመዶች ብዙ ናቸው፤ ወደ ተስፋ ምድር እንዳንሻገር የሚጎትቱ ሰበቦች ሞልተዋል፤ ዳሩ ግን ከሕማማቱ ወዲያ ትንሣኤ ከዕንቅፋቱ ባሻገር ስኬት እንደሚጠብቀን አምነን እንታገላለን ሲሉም አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ትንሣኤ መቃረቧን ገልፀው፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ከሚበሰርባቸው ምዕራፎች አንዱ ግንቦት ላይ የሚካሄደው ምርጫ መሆኑንም አመላክተዋል። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም ብለዋል። • የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሁለት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ካደረጉት የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት ኢቫሪስቴ ንድያይሺሚዬ ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን ባሳለፍነው ሳምንት ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ለማጠናከር ያለሙ በርካታ የመግባቢያ ሰነዶች ፊርማ አከናውነናል ሲሉም አስታውቀዋል። ስምምነቶቹ ለሁለቱም ሀገራት የበለጸገ እና የተባበረ መጻኢ ዕድልን የሚያረጋግጡ የቆዩ ግንኙነቶቻችንን ወደ ተጨባጭ ትብብር ለመቀየር እንደ ወሳኝ መሠረት የሚያገለግሉ የጋራ ቁርጠኝነታችን ማሳያ ጭምር ናቸው ብለዋል። ጉብኝታቸውን እንዳጠናቀቁም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪኤግዚም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኢሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም ስትራቴጂካዊ ግንኙነታችንን በምናጠናክርባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረናል ብለዋል። • የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደር ዓመታዊ አፈጻጸም ግምገማ ባሳላፍነው ማክሰኞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደር ፕሬዚዳንት ሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማ እና ውይይት አድርገዋል። • የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ሹመት መራዘም በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 62(9) እና በዐዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀፅ 2(ለ) መሠረት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አሥተዳደርን በርዕሰ መሥተዳደርነት እንዲመሩ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አሥተዳደር አስመልክቶ በጸደቀው ደንብ ቁጥር 479/2013 አንቀጽ 4(2) እና የዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ባቀረቡት መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደን ሹመት ለአንድ ዓመት አራዝመዋል። • ማዕድ ማጋራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል። • የአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ኅልፈተ ሕይወት አምባሳደር ቆንጅት፤ በዲፕሎማሲው መስክ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ላበረከቱት ጉልኅ አስተዋጽዖ፣ ለሰጡት አስተምኅሮና ለነበራቸው ብልኅ አመራር ምንጊዜም ሲታወሱ እንደሚኖሩ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት ገልጸዋል። ትጉኅና ከብረት የጠነከሩ ዲፕሎማት ነበሩ በማለት ለሙያቸው የነበራቸውን ጽኑ አቋምና የሀገር ፍቅር ስሜትም አንስተዋል። ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት በማረፋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሰማቸውን ኀዘን ገልጸዋል። አምባሳደሯ ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል ብለዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት፤ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ እና ታላቅ ዐሻራን ማሳረፍ የቻሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ጥልቅ ኀዘን ተሰምቶኛል ብለዋል። አምባሳደር ቆንጂት እስከ ከፍተኛ ዲፕሎማትነት በደረሰ ረጅም የሥራ ዘመናቸው ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ያስመዘገቡት ድል እና ያበረከቱት አስተዋጽዖ ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ባሳለፍነው ሳምንት “ፖሊሳዊ አንድነት ለዘላቂ ሰላም” በሚል መሪ ሐሳብ 20ኛው የፖሊስ ኮሚሽነሮች መክፈቻ ጉባዔ ተካሂዷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፤ የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያ ፖሊስ በሚሰጠው አገልግሎት ታማኝም አሳማኝም መሆን አለበት ብሎ ያምናል ብለዋል። የፖሊስ ኃይላችን የጥፋት ኃይሎች በሀገራችንና በሕዝባችን ላይ የሰነዘሩትን ጥቃት በአንድነት በመቆምና መስዋዕትነት በመክፈል ቀልብሷል፤ ይህም ለሁላችንም ኩራት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የፖሊስ አመራሮችና የሠራዊቱ አባላት በዕውቀት፣ በታማኝነትና በሕዝብ አገልጋይነት ሥነ-ልቦና ለላቀ ተልዕኮ እንድትዘጋጁ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3904
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2658
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8448
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6936
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60887
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54889
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35384
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33002
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27990
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27254
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26743
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26306
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60887
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54889
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35384
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33002
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 509
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ
Apr 12, 2026 995
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ በቀበኔሳ ገቢሳ ትንሣኤ ለሰው ልጅ ተስፋን፣ ዘለዓለማዊ ሕይወትን እና ከኃጢአት ነፃ መውጣትን የሚያበስር ኃይማኖታዊ በዓል ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ በመነሳቱ የሰው ልጅ የዘለዓለም የሕይወት አክሊልን ተስፋ ያደረገበት፣ የእግዚአብሔር ፍቅር የተገለጠበት እንዲሁም የሰው ልጅ ከዘለዓለም ሞትና ከኃጢአት ባርነት ነፃ የወጣበት የድኅነት፣ የፍቅር፣ የጽናትና የተስፋ ብርሃን ብስራት ነው፡፡ የትንሣኤ በዓል ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የመነሳቱ ታላቅ ምሥጢር የሚታሰብበት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ የሰው ልጅ ከውርደት ወደ ክብር፣ ከኃጢያት ባርነት ወደ ድኅነት እንዲሁም ከጉስቁልና ወደ ብሩህ ተስፋ የተሸጋገረበት የድል አዋጅ ነው። በዕለቱም በሞት ላይ ሕይወት፣ በሐዘን ላይ ደስታ፣ በቂም ላይ ይቅርታ ተበስሮበታል። ከበዓላት ሁሉ የላቀ የነጻነት ተምሳሌት ነው ትንሣኤ። 👉የትንሣኤ ሕያው አስተምሮ በዕለት ተዕለት ሕይወት ትንሣኤ ሲከበር ከሥርዓተ አምልኮ ባለፈ፣ በዓሉ የሚሰጠውን ታላቅ አስተምሮ ማጤን ይገባል። ትንሣኤ በየቀኑ ካለንበት ድካምና ውድቀት በአዲስ መንፈስ የመነሳት አቅም ነው። በዓሉ የሚያስተምረንን የጽናት፣ የተስፋና የአብሮነት ዕሴት በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ መኖር ያስፈልጋል። ለዚህም የተቸገሩን መርዳት፣ የታመሙትን መጠየቅና የተጣሉትን ማስታረቅ የበዓሉን ትርጉም እውነተኛ ያደርገዋል። 👉የኢትዮጵያ ትንሣኤ፤ በፈተና የጸና ብርሃን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዓሉን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የዘንድሮውን የትንሣኤ በዓል የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በፈታኝ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ሆና እያለች ነው። መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችንም እሾህ የበዛበት ሊሆን ይችላል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ፣ በጨለማ ወጥመድ ሊያሥሩን የሚሞክሩ መሰናክሎች ቢበዙም፣ እምነታችን ግን ከሕማማት በኋላ ትንሣኤ እንደሚመጣ ነው" ብለዋል፡፡ "ኢትዮጵያ ዛሬም ትንሳኤዋን እያየች ነው። መቃብሯ ተከፍቷል፤ ማኅተሙም ተሰብሯል። የትንሣኤውን ዜና ሊያደበዝዙ የሚሞክሩ የውሸት ወሬዎችና ተስፋ አስቆራጭ ትረካዎች የሀገራችንን የብርሃን ጉዞ ሊገቱት አይችሉም። ትንሳኤው እውነት ነው፤ ብርሃኑም የማይቀለበስ ሀቅ ሆኗል" ሲሉም አረጋግጠዋል፡፡ 👉ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ ምክክር፤ የተስፋ ምዕራፎች የኢትዮጵያ ትንሣኤ አንዱ መገለጫ ዴሞክራሲን የመገንባት ጽናት ነው። ትንሣኤ ያለ ሕማማት እንደማይገኝ ሁሉ ዴሞክራሲ ያለ ፈተና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ዴሞክራሲ የሚገነባው በጽናት እንጂ በፍርሃት አይደለም። ዴሞክራሲን እየገነባን በትዕግሥትና በቆራጥነት ወደ ተስፋዋ ምድር እንደርሳለን። አሁን ያለው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጦርነት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና ማህበራዊ አለመረጋጋት የትንሳኤን ትምህርት ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊ ያደርገዋል፡፡ ችግሮችን በብቸኝነት የምንወጣበት ጊዜ አብቅቷል። ዛሬ እንደህዝብ የሚያስፈልገን ከ"እኔ" ወደ "እኛ" መሸጋገር፣ የግል ፍላጎትን ለጋራ ስኬት መስዋዕት ማድረግ ግድ የሚልበት ወቅት ላይ ነን። የአንድነት ጉዟችንን በማጠናከር ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ጫናዎችን ለመቋቋም በጋራ መቆም ይገባናል። የተቸገሩትን በመርዳት፣ የታመሙትን በመጠየቅና የተጣሉትን በማስታረቅ የተግባር አብሮነትን በማሳየት የበዓሉን እውነተኛ ትርጉም መግለጥ ይገባል፡፡ 👉ምርጫ፤ ከኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበትና ተስፋ የታደሰበት ዕለት ነው። እኛም በምርጫ ካርዳችን የሃሳብ ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ አንድነት ድል በማድረግ የኢትዮጵያን የብልፅግና ትንሳኤ እናረጋግጣለን። በትንሣኤ በዓል የምንማረው ይቅርታና ጽናትም ለምርጫችን ስኬት አቅም ይሆናል። በኅብረት የምንሰጠው ድምፅም የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የመቅረጽ ኃይል በእጃችን መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው "ምርጫ የኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ነው። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም። በዓለም ላይ በደልዳላ መንገድ ተጉዞ ዴሞክራሲን የገነባ ሀገር የለም። ዴሞክራሲና ብልፅግና ያለ ጽናት አይሳኩም። ከእኛ በፊት ዐመጻውን በትዕግሥት የመከቱ ተሻግረዋል፤ ሑካታውን በጽናት ያለፉ አሳክተዋል። ብንመኝም ፈተናውን አናስቀርም፤ መጽናት ግን እንችላለን። ከድኅነት መውጫው ብርታታችን፣ ወደ ዴሞክራሲ መድረሻችው ትዕግሥታችን እንደሆነ አምነን ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በሙሉ ልባችን እንትጋ!!" ብለዋል። 👉የወደፊት እጣ ፈንታችን በእጃችን ከፊታችን የሚጠብቁን ሀገራዊ ምክክርና የ2018 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የወደፊት መጻኢ ዕድል የሚወስኑ ታላላቅ ሁነቶች ናቸው። እነዚህ ሂደቶች ስኬታማ የሚሆኑት እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን ሲወጣ ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በልባችን ውስጥ ይቅርታና አብሮነት ሲነግስ ብቻ ግቡን ይመታል። ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበት እንደሆነው ሁሉ፣ በምክክሩም ጥልን፣ ጥርጣሬን፣ ያለመግባባት መንፈስን ድል መንሳት ይገባል፤ ቅንነት፣ ተስፋና መተሳሰብ ለምክክሩ ስኬት የመተማመኛ ቁልፎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ 2018 ዓ.ም ደግሞ የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ ማሳያ አንጓ ነው፤ የዜጎች ነፃ ተሳትፎ መብታቸውን የሚያስከብሩበት ፍላጎታቸውን የሚያረጋግጡበት ማረጋገጫ ማህተም ጭምር፡፡ ዜጎች የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን የሚያስከብሩበት፤ የሌላውን ሃሳብ አክብረው የራሳቸውን የሚያስከብሩበት ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በጋራ የሚቆሙበት መድረክ ነው፡፡ ትንሣኤ የድልና የነጻነት በዓል ነው። ይህንን ታላቅ ዕለት ስናከብር ያለፈውን ቁስል ሽረን፣ ለነገ ተስፋ ሰንቀን መሆን አለበት። እርስ በእርስ በመደጋገፍ፣ ችግሮችን በንግግር በመፍታት ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ስኬታማነት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል። የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ እንቁም! መልካም የትንሳኤ በዓል!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም