ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Aug 4, 2026 32
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት ዛሬ የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረውን ፋይዳቨርስን በይፋ ሥራ አስጀምረናል ብለዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ወደ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎችን በመመዝገብ፣ ከ160 ሚሊዮን በላይ የማረጋገጫ አገልግሎቶችን በመስጠትና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ የዲጂታል ኢኮኖሚያችን የጀርባ አጥንት መሆኑን አስመስክሯል ነው ያሉት። ዛሬ ደግሞ ይህ ስኬታችን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ተሸጋግሮ፣ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር ፋይዳቨርስ በሚል ስያሜ ራሱን የቻለ የመንግስት የልማት ድርጅት በመሆን ወደ ስራ ገብቷል ብለዋል። ይህ ውሳኔ ዲጂታል ማንነት ልክ እንደ መንገድ፣ ኃይል እና ቴሌኮሙኒኬሽን ሁሉ ለሀገራችን ተወዳዳሪነትና ዘላቂ እድገት ወሳኝ የሆነ ስትራቴጂካዊ ሀገራዊ መሰረተ ልማት መሆኑን ማረጋገጫችን ነው ሲሉ ገልጸዋል። ከሀገር አልፎ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሰረት ለቀጣናው እና ለአፍሪካ አህጉር ልምድና አቅም በማጋራት የአፍሪካ የዲጂታል ሽግግር መሪ እንድንሆን ያስችለናል። የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዟችን ስኬት የሚለካው በደረስንባቸው ቴክኖሎጂዎች ሳይሆን፣ ሕዝባችን እነዚህን ውጤቶች የራሱ አድርጎ ሲጠቀምባቸው እና ህይወቱ ሲለወጥ ነው። የቴክኖሎጂ አቅርቦታችንን ጥራት በመጠበቅ፣ የዳታ ደህንነታችንን በማረጋገጥ እና የዜጎቻችንን ዲጂታል ግንዛቤ በማሳደግ የያዝነውን አቅጣጫ በበለጠ ቁርጠኝነት እንቀጥላለን ብለዋል።
የመደመር መንግሥት የዲጂታል መሠረተ ልማት እመርታ የዜጎችን ተጠቃሚነት እያሳለጠ ነው - ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)
Aug 4, 2026 35
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት በዲጂታል መሠረተ ልማት ያስመዘገበው እመርታ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳለጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ፋይዳ) በመንግሥት የልማት ድርጅትነት እንደገና ተደራጅቶ "ፋይዳ ቨርስ ዲጂታል ሶሉሽንስ ኢንተርፕራይዝ" በሚል ስያሜ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሥር ተካቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው የ"ፋይዳ ቨርስ" ይፋዊ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ፋይዳ ቨርስ የኢትዮጵያን የዲጂታል ዘመን ጥንካሬ፣ ዘላቂነትና በዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ያጎለብታል ብለዋል። ባለፉት ስምንት ዓመታት የመደመር መንግሥት የቴሌኮሙኒኬሽን መሠረተ ልማትን በማጠናከር በድምፅና በኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን ገልጸዋል። የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎቶችም የመንግሥትን አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት እያሳደጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። የፋይዳ አገልግሎት በአፍሪካ ከፍጥነት የዲጂታል ማንነት ሥርዓቶች አንዱ እየሆነ ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ፋይዳ ቨርስ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስን መቀላቀሉም ተቋማዊ ጥንካሬን ይፈጥራል ብለዋል። የኢትዮጵያ የሕዝብ መሠረተ ልማት የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅምና ልምድም ደኅንነቱ የተጠበቀ የዲጂታል ማንነት ሥርዓት በመገንባት በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት እየሳበ መሆኑን አንስተዋል። የፋይዳ ቨርስ ዲጂታል ሶሉሽንስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዮዳሄ አርዓያሥላሴ በበኩላቸው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ የዜጎችን ማንነት በዲጂታል መንገድ የመመዝገብና የማረጋገጥ ሰፊ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም በአዲስ መልክ "ፋይዳ ቨርስ ዲጂታል ሶሉሽንስ" በሚል ወደ የመንግሥት የልማት ድርጅት ማደጉም የዲጂታል ውጤታማነትን የበለጠ ለማጎልበት የተወሰደ ስትራቴጂያዊ እርምጃ መሆኑን አስረድተዋል። ተቋማዊ ሽግግሩም በራስ አቅም የቴክኖሎጂ ፈጠራንና ዘላቂ የፋይናንስ መሠረትን በማጣመር ወደ ተሻለ የዲጂታል አገልግሎትና የንግድ ሥርዓት ለመሸጋገር የተዘጋጀ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል። በዲጂታል ማንነት መሠረተ ልማት የተፈጠረው አቅም ለፈጠራ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለፋይናንስ አካታችነትና ለዘመናዊ የመንግሥት አገልግሎቶች ጠንካራ መሠረት እንደሚሆንም አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ የዲጂታል ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Aug 4, 2026 51
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዲጂታል ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው የ"ፋይዳቨርስ" ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፤ የ"ፋይዳቨርስ" ሥራ መጀመር ኢትዮጵያ ለዲጂታል ሉዓላዊነቷ የሰጠችውን ከፍተኛ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራሙ ለሀገሪቱ የዲጂታል ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ሆኖ መገንባቱን ጠቅሰው፤ እስካሁን ወደ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ይህም ከ13 ሚሊዮን በላይ የብሔራዊ መታወቂያ ካርዶች ታትመው መሰራጨታቸው፣ ከ160 ሚሊዮን በላይ የማንነት ማረጋገጫ አገልግሎቶች መሰጠታቸውና በ13 ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች የዲጂታል ማንነት መሠረተ ልማት መዘርጋቱን አስረድተዋል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራሙ እንደ መንግሥት የልማት ድርጅት በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር "ፋይዳቨርስ" በሚል ስያሜ እንደገና መደራጀቱን ገልጸዋል። ፕሮግራሙም የኢትዮጵያ ይፋዊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ማዕከል ሆኖ እንደሚያገለግል ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ እ.አ.አ. በ2030 የኢትዮጵያን ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በ6 በመቶ እንዲያሳድግና በቢሊዮኖች ዶላር የሚለካ ቀጥተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዲያመጣ ትልቅ ተስፋ እንደተጣለበት ገልጸዋል። አገልግሎቱ ከነባሩ Fayda ID መተግበሪያ በተሻሻለ መልኩ በFaydaPass አፕሊኬሽን እና በሌሎች ዘመናዊ ዲጂታል ምርቶች የቀረበ በመሆኑ የአገልግሎቱን ተደራሽነትና የመፍትሔ አቅም በእጅጉ እንደሚያሳድግ አስገንዝበዋል። ዳታ በዘመናችን የኢኮኖሚና የሉዓላዊነት ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ፣ የሀገራዊ መረጃዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ ዘመናዊ የሳይበር ደህንነት ቴክኖሎጂዎችን እና ጠንካራ የዳታ አስተዳደር ፖሊሲዎችን በተከታታይ መተግበር እንደሚገባ አክለዋል። ቴክኖሎጂ በገጠርና በከተማ የሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያገናኝ፣ የአገልግሎት ተደራሽነትን የሚያሰፋና ድህነትን ለመቀነስ የሚያግዝ መሆን እንዳለበት አስረድተዋል። የዜጎችን የዲጂታል ግንዛቤ ማሳደግ የስትራቴጂው ዋነኛ አካል መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ መሠረት የዲጂታል መሠረተ ልማት ልምድን ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማጋራት የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ይህም ለአህጉራዊ ትብብርና የዲጂታል ዲፕሎማሲ ጠንካራ መሠረት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እንደ ሀገሪቱ የሉዓላዊ ሀብት ፈንድ ሀገራዊ ሀብቶችን በብቃት ለማስተዳደር እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። "ፋይዳቨርስ" ወደዚህ ቤተሰብ መቀላቀሉም ዲጂታል ማንነት ልክ እንደ መንገድ፣ ኃይልና ቴሌኮሙኒኬሽን ወሳኝ ስትራቴጂካዊ መሠረተ ልማት መሆኑን የሚያረጋግጥ ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል። ይህ ስኬት እውን እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ የተቋሙ አመራሮች፣ ሠራተኞችና የልማት አጋሮች ምስጋና አቅርበዋል።
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 67
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።
የተጠናቀቀው በጀት ዓመት አዲስ አበባ የዜጎችን ማህበራዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ እመርታዊ ውጤቶችን ያስመዘገበችበት ነው
Aug 4, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት አዲስ አበባ የዜጎችን ማህበራዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ እመርታዊ ውጤቶችን ያስመዘገበችበት ዓመት መሆኑ ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ልማት ክላስተር አፈጻጸምና በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊና የማህበራዊ ልማት ክላስተር አስተባባሪ ተወካይ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ እንዳሉት፤ ክላስተሩ በ2018 በጀት ዓመት በቅንጅት የተመሩ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን አከናውኗል። በአንድ ተቋም ብቻ ተጀምረው ሊጠናቀቁ የማይችሉና የሌሎች ተቋማትን ትብብር የሚሹ ሥራዎች በጋራ ታቅደው፣ በጋራ ተገምግመው በውጤታማነት መከናወናቸውንም አስታውቀዋል። በዚሁ መሠረት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በጤና፣ በትምህርትና በሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ተግባራት በቅንጅት በውጤታማነት መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ይህ የቅንጅት አሠራር ለሁሉም ተቋማት አቅም የሚፈጥርና መልካም ተሞክሮ በመሆኑ፣ በቀጣይም በሁሉም ዘርፎች ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ፤ በትምህርት ዘመኑ የተመዘገቡ ስኬቶች እንዲሳኩ የማህበራዊ ልማት ክላስተሩ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ገልጸዋል። ክላስተሩ ከተማሪዎች ጤና፣ ምገባ፣ ትምህርትና ሥልጠና ጥራትና ቁጥጥር ጋር ተያይዘው የሚከናወኑ ተግባራትን በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመዋል። በዚህም በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በሁሉም የትምህርት ተቋማት የተረጋጋ፣ ሰላማዊና ምቹ የመማርና የማስተማር ሂደት እንዲኖር ማስቻሉን ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የተቋማት ክትትል ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሞላ ንጉሥ በበኩላቸው፣ በበጀት ዓመቱ በማክበራዊ ዘርፍ እመርታዊ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። በ2019 በጀት ዓመትም የተመዘገቡ እመርታዊ ውጤቶችን በማስቀጠል የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የተቋማቱ የቅንጅት አሠራር በቀጣይም በተጠናከረ መልኩ በመቀጠል የከተማዋን ማህበራዊ አገልግሎቶች የበለጠ ውጤታማና ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 67
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።
በምክክር ጉባኤው ልዩነቶችን በምክክር በመፍታት ሀገራዊ መግባባት የሚፈጥሩ ምክረ-ሃሳቦች ይጠበቃሉ - ተመካካሪዎች
Aug 4, 2026 159
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ልዩነቶችን በምክክር በመፍታት ዘላቂ ሰላምና ሀገራዊ መግባባት የሚፈጥሩ ምክረ-ሃሳቦች እንደሚጠበቁ ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ዋናው የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት በዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ነው፡፡ ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ኦንጎላይ ጎሻንዶ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ ትክክለኛና የማያሻማ ዘላቂ ሰላም መፍጠር የሚያስችል ትልቅ ተስፋ ያነገበ ነው፡፡ የተለያዩ አመለካከቶችና ሀሳቦችን በነጻነት በማንፀባረቅ ለመጪው ትውልድ የተሻለችና የተረጋጋች ሀገር ለመገንባት ጉባኤው መሰረት ይጥላል ብለዋል፡፡ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ሳሮን አመነው በበኩሏ፤ መድረኩ የመላ ኢትዮጵያውያን አስተሳሰብ በግልጽ የተንጸባረቀበት መሆኑን ገልጻለች። ተመካካሪዎች ሀሳባቸውን በነፃነት በመግለጽ ልዩነቶችን እያጠበቡ ወደ ጋራ መግባባት መምጣት የሚችሉበት መሆኑን ተናገራለች፡፡ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ የህዝብና አደረጃጀቶች ተወካይ ተመካካሪዎች በአንድ መድረክ መገናኘታቸው ሀገራዊ አንድነትን ይበልጥ ይገነባል የያሉት ደግሞ አቶ ስርዓት ደንግሬቲ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያውያን በተወካዮቻቸው አማካኝነት በጋራ መምከራቸው የጋራ ሀገራቸውን በአንድነት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት በማጽናትና የጸረ ሰላም ኃይሎችን ከንቱ ዓላማ በማምከን የሚያኮራ ተግባር እየፈጸመ ነው - ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል መላኩ ፋንታ
Aug 2, 2026 864
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ፖሊስ የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት በማጽናትና የጸረ ሰላም ኃይሎችን ከንቱ ዓላማ በማምከን የሚያኮራ ተግባር እየፈጸመ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል መላኩ ፋንታ ገለጹ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሥራ ክፍሎች፣ አመራሮች፣ አባላትና ባለድርሻ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ፣ የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ፣ የፖሊስ አመራሮች፣ አባላትና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ በዚሁ ወቅት፤ አዲስ አበባ በተከናወኑ ልማቶች ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ በአፍሪካ ተጠቃሽ ከተማ እየሆነች መምጣቷን ገልጸዋል። ይህ እውን እንዲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሌሎች የጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ የጎላ ሚና መጫወቱንም አድንቀዋል። መንግሥት ዜጎችን በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን ጥረቶች ለማሰናከል የሚንቀሳቀሱ የጸረ ሰላም ኃይሎች ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመተባበር እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ በተቀናጀ የአሰራር ሥርዓት የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት በማጽናትና የጸረ ሰላም ኃይሎችን ከንቱ ዓላማ በማምከን ያስመዘገበው ውጤት የሚያኮራ ነው ብለዋል። በመሆኑም መላው የአዲስ አበባ ፖሊስ አመራርና አባላት የጸረ ሰላም ኃይሎችን ተልዕኮ በማክሸፍ የተገኘውን ስኬት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪም ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከል እና ወንጀል ሲፈጸም ፈጣንና ውጤታማ ምላሽ በመስጠት ረገድ የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ከህብረተሰቡ እና ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል - የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
Aug 2, 2026 697
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት ከህብረተሰቡ እና ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራትን ማከናወኑን አስታወቀ። ዋና ጠቅላይ መምሪያው በ2018 ዓ.ም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የስራ ክፍሎች አመራርና እና አባላት እንዲሁም ተቋሙ ስኬታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና ምስጋና መርሃ ግብር እያካሄደ ነው። በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ባለው መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ፣ የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ሊዲያ ግርማ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ፣ የፖሊስ አመራር እና አባላትን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ጠቅላይ መምሪያው ከህዝቡ እና ሌሎች ፀጥታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራት አከናውኗል። ዓመቱ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫን ጨምሮ ትላልቅ አህጉራዊ ኹነቶች የተካሄዱበት መሆኑን አስታውሰው፤ ኹነቶቹ በስኬት እንዲካሄዱ የከተማው ፖሊስ ከተለያዩ የጸጥታ ተቋማት ጋር በጋራ በመሆን አመርቂ ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል። በማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገለግሎት ህዝቡን ተሳታፊ በማድረግ ስኬታማ ስራ መከናወኑን ገልጸው፤ በዚህም የመዲናዋን ሰላም በማጽናት ረገድም ተጠቃሽ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል። ዋና ጠቅላይ መምሪያው የፖሊስ አባላቱን ውጤታማነት ይበልጥ የሚያልቁ አሰራሮችን እየተገበረ መሆኑን አስታውቀዋል። ለፖሊስ አባላት መኖሪያ የሚሆን ባለ 15 ወለል ህንጻዎች ግንባታ መጀመሩን አስታውሰው፤ የዋና መምሪያው ቢሮ ዕድሳትም በቅርቡ ይጠናቀቃል ብለዋል። የዛሬው የእውቅናና ምስጋና መርሃ ግብር በቀጣይም የሚከወኑ ስራዎች በላቀ ተነሳሽነት እንዲሰሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
የምክክር ጉባኤው የጋራ መግባባትን የሚገነባ ለአፍሪካም ተምሳሌት የሚሆን ታሪካዊ ሂደት ነው
Aug 2, 2026 703
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ጠንካራ ሀገረ መንግሥትና የጋራ መግባባትን የሚገነባ ለአፍሪካም ጭምር ተምሳሌት የሚሆን ታሪካዊ ሂደት መሆኑን ፖለቲከኞች ገለጹ። ዋናው የምክክር ጉባኤ በ4 ሺህ የሀገር ውስጥና የውጭ ዜጎች የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች መካከል ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ፖለቲከኛው አበራ በቀለ ለኢዜአ እንዳሉት፤የምክክር ጉባኤው ለዘመናት ሲቆዩ በነበሩ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ መሠረታዊ ሀገራዊ አለመግባባቶች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተከፈተ ታሪካዊ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። በጉባኤው የሕዝብ ውክልና የተሰጣቸው ተመካካሪዎችም ለዘመናት ሲጠበቅ የነበረውን ታሪካዊ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም የጋራ መግባባትን ለመፍጠር መድረኩን ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የምክክር ሂደቱ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ችግሮቻቸውን በራሳቸው አቅምና በምክክር መፍታት እንደሚችሉ የሚያሳይ በመሆኑ ለአፍሪካም ጠቃሚ ተሞክሮና ትምህርት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያን ችግሮች በራሷ መንገድ በጋራ መግባባት መፍትሔ የምትሰጥ ሀገር ስትሆን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎቷን የምታስጠብቅ ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደሚያስችል ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና ፖለቲከኛ አብርሃም በርታ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ የምክክር ጉባኤው ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር ሰላምን፣ ብሔራዊ ደህንነትንና ልማትን ለማፋጠን ከፍተኛ ፋይዳ አለው። አሁን እየተካሄደ ያለው የምክክር ሂደት የይስሙላ ሳይሆን ለረጅም ጊዜ የቆዩ መሠረታዊ ሀገራዊ ችግሮችን በተጨባጭ ለመፍታት የታለመ መሆኑን አስረድተዋል። የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች አካታችና አሳታፊነትም ሁሉም ዜጋ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎችና ችግሮች በማንጸባረቅ የጋራ ሀገራዊ መግባባትና አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ፖለቲከኞቹ እንደገለጹት፤ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን ችግሮች በዜጎቿ ምክክርና መግባባት ለመፍታት የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል ከመሆኑም በላይ የፓን አፍሪካኒዝምን እሳቤ በተግባር የሚያንጸባርቅ ሂደት መሆኑን አመልክተዋል። ይህም አፍሪካውያን ችግሮቻቸውን በራሳቸው አቅምና ችሎታ መፍታት እንደሚችሉ ጠንካራ መልዕክት የሚያስተላልፍ መሆኑን ጠቅሰዋል። የምክክሩ ውጤትም ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለቀጣናውና ለመላው አፍሪካ በሰላም ግንባታ፣ በልማትና በጋራ መግባባት ረገድ ጠቃሚ ተሞክሮ እንደሚሆን ገልጸዋል። በተጨማሪም ልዩነቶችን በኃይል ሳይሆን በውይይትና በሃሳብ የበላይነት የመፍታት የሰላም ባህልን በማጠናከር፣ ለቀጣዩ ትውልድ ተምሳሌት የሚሆን ጠቃሚ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
ሀገራዊ ምክክር ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሀገራዊ መግባባት ወርቃማ ዕድል ነው
Aug 2, 2026 736
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 26/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ የምክክር መድረክ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና የጋራ መግባባት ወርቃማ ዕድል መሆኑን ተመካካሪ ሌተናል ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መጀመሩ ይታወቃል። በጉባኤው ላይ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በመሳተፍ በአሁኑ ወቅት በዓበይት ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ይህ ሀገራዊ የምክክር ሂደት ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም፣ አብሮነት እና የጋራ መግባባት መረጋገጥ እጅግ ታላቅ ተስፋ የተጣለበት መድረክ ሆኗል። ተመካካሪ ሌተናል ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል፣ በምክክር ሂደቱ በከፍተኛ ደስታና አክብሮት እየተሳተፉበት እንደሚገኙ ገልጸዋል። አራት ሺህ ተመካካሪዎች ለሀገሪቱ ሰላም እና የጋራ መግባባት የሀሳብ ፊት አውራሪ ሆነው እንደሚወጡ ትልቅ እምነት እንዳላቸው አንስተዋል። በመድረኩ ተመካካሪዎች ሀሳባቸውን በግልጽ በማንጸባረቅ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው፣ ከዚህ አሳታፊ ሂደት ትልቅ ትምህርት እና ልምድ መቅሰም እንደሚቻል አስገንዝበዋል። መድረኩ የመሸናነፍ ሳይሆን ሀገራዊ መግባባት የሚገነባበት ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ይህንን ታሪካዊ የምክክር ሂደት ተስፋ የጣሉበት መሆኑን አንስተዋል። ሰላማዊ የመፍትሔ ማዕድ በሆነው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሰባስቦ መመካከር የተሻለ እና የሰለጠነ አካሄድ መሆኑንም ተናግረዋል። የየትኛውም አካባቢ ችግር የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ፣ በጋራ መግባባት እና በአብሮነት መንፈስ የጋራ መፍትሔ ማበጀት እንደሚቻልም አስረድተዋል። ይህ ሀገራዊ የምክክር ሂደት በተለይም ልሂቃን በዘመናቸው ያካበቱትን ልምድ፣ ያነበቡትን እና ያወቁትን ወደ መሬት አውርደው ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚኖራቸውን አዎንታዊ ሚና የሚያበረክቱበት ወርቃማ ዕድል ነው ብለዋል። በመሆኑም ያላቸውን ሀሳብ ሰብሰብ አድርገው ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና አብሮነት አስተማማኝ መሠረት እንዲጥሉ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።
የምክክር ጉባኤው ለኢትዮጵያ አዲስ የምክክር ልምምድን የከፈተ ታሪካዊ ዕድል ነው
Aug 2, 2026 819
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 26/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለኢትዮጵያ አዲስ የምክክር ልምምድን የከፈተ ታሪካዊ ዕድል መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የፖለቲካ ፓርቲ ተወካይ ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ በጉባኤው የግልና የቡድን ፍላጎቶችን በማጥበብ ሀገራዊ ጥቅምን በማስቀደም፣ በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ ነፃና አሳታፊ ምክክር እየተካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለኢትዮጵያ አዲስ የምክክር ልምምድን የከፈተ ታሪካዊ ዕድል መሆኑንም የፖለቲካ ፓርቲ ተወካይ ተመካካሪዎች ገልጸዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ (አብን) ተወካይና ተመካካሪ ጣሂር መሐመድ እንዳሉት፤ በምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ምክክር እየተደረገ ነው። በዋናው የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይትና ንዑሳን አጀንዳዎችም በተመካካሪዎች መካከል በነፃነትና አካታችነት እየተመከረባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን መሠረታዊና መዋቅራዊ ችግሮች በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ መግባባት በመፍጠር መፍትሔ የሚሰጥ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል። የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ትዴፓ) ሊቀመንበርና ተመካካሪ አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የመደማመጥና የመግባባት ባህልን በማጠናከር በተሻለ አሳታፊነት እየተካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ከአጀንዳ ማሰባሰብና ከተሳታፊዎች ልየታ ሂደት ጀምሮ አሳታፊነትንና አካታችነትን በተግባር በማረጋገጥ ውጤታማ ሥራ መሠራቱንም አስታውሰዋል። ከአራቱም የሀገሪቱ ማዕዘናት ሕዝብን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በዋናው የምክክር ጉባኤ ላይ ሃሳባቸውን በነፃነት በማንሸራሸርና በግልጽ ተሳትፎ ተስፋ ሰጪ ምክክር እያካሄዱ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀገራዊ ችግሮችን በሰለጠነ ምክክር ለመፍታት፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ ለመምከርና ዘላቂ የሆነ መግባባት ለመፍጠር የተገኘ ታሪካዊ ዕድል መሆኑን ጠቁመዋል። የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) አባልና የጉባኤው ተመካካሪ ሙሐሙድ መሐመድ ሀሰን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች የኢትዮጵያን ብዝኅነት፣ ሕብረ-ብሔራዊ እሴቶችና የጋራ ሀገራዊ ጥቅሞችን በሚያንጸባርቁ ሃሳቦች ላይ እንዲመክሩ ዕድል ፈጥሯል። ሀገራዊ አለመግባባቶችን በጦር መሣሪያ በታገዘ ግጭትና በኃይል ለመፍታት መሞከር ዘላቂ መፍትሔ የማያማጣና አዋጭ ያልሆነ አካሄድ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህም የጋራ ሀገርን በመገንባት አዲስ የምክክር ታሪክ እየጻፍን ነው ያሉት አቶ ሙሐሙድ፤ የጉባኤው አጀንዳዎች ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ የመግባባት ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ተመካካሪ ገነነ ገረቡ በበኩላቸው፤ በምክክር ጉባኤው አንዱ የሌላውን ሃሳብ መረዳት በሚያስችል መልኩ ማንኛውም የሕዝብ አጀንዳ በነፃነት እየተንጸባረቀ ነው ብለዋል። የምክክር ጉባኤውም ለዘመናት የቆዩ የአለመግባባቶችን ለቀጣዩ ትውልድ እንዳይተላለፉ ለማድረግ ስልጡን ምክክር እያደረግን ነው ብለዋል። በተመካካሪዎች መካከልም በአርአያነት የሚወሰድ ነፃ ምክክር እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
ፖለቲካ
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 67
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።
በምክክር ጉባኤው ልዩነቶችን በምክክር በመፍታት ሀገራዊ መግባባት የሚፈጥሩ ምክረ-ሃሳቦች ይጠበቃሉ - ተመካካሪዎች
Aug 4, 2026 159
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ልዩነቶችን በምክክር በመፍታት ዘላቂ ሰላምና ሀገራዊ መግባባት የሚፈጥሩ ምክረ-ሃሳቦች እንደሚጠበቁ ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ዋናው የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት በዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ነው፡፡ ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ኦንጎላይ ጎሻንዶ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ ትክክለኛና የማያሻማ ዘላቂ ሰላም መፍጠር የሚያስችል ትልቅ ተስፋ ያነገበ ነው፡፡ የተለያዩ አመለካከቶችና ሀሳቦችን በነጻነት በማንፀባረቅ ለመጪው ትውልድ የተሻለችና የተረጋጋች ሀገር ለመገንባት ጉባኤው መሰረት ይጥላል ብለዋል፡፡ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ሳሮን አመነው በበኩሏ፤ መድረኩ የመላ ኢትዮጵያውያን አስተሳሰብ በግልጽ የተንጸባረቀበት መሆኑን ገልጻለች። ተመካካሪዎች ሀሳባቸውን በነፃነት በመግለጽ ልዩነቶችን እያጠበቡ ወደ ጋራ መግባባት መምጣት የሚችሉበት መሆኑን ተናገራለች፡፡ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ የህዝብና አደረጃጀቶች ተወካይ ተመካካሪዎች በአንድ መድረክ መገናኘታቸው ሀገራዊ አንድነትን ይበልጥ ይገነባል የያሉት ደግሞ አቶ ስርዓት ደንግሬቲ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያውያን በተወካዮቻቸው አማካኝነት በጋራ መምከራቸው የጋራ ሀገራቸውን በአንድነት ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት በማጽናትና የጸረ ሰላም ኃይሎችን ከንቱ ዓላማ በማምከን የሚያኮራ ተግባር እየፈጸመ ነው - ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል መላኩ ፋንታ
Aug 2, 2026 864
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ፖሊስ የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት በማጽናትና የጸረ ሰላም ኃይሎችን ከንቱ ዓላማ በማምከን የሚያኮራ ተግባር እየፈጸመ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል መላኩ ፋንታ ገለጹ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሥራ ክፍሎች፣ አመራሮች፣ አባላትና ባለድርሻ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ፣ የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ፣ የፖሊስ አመራሮች፣ አባላትና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ በዚሁ ወቅት፤ አዲስ አበባ በተከናወኑ ልማቶች ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ በአፍሪካ ተጠቃሽ ከተማ እየሆነች መምጣቷን ገልጸዋል። ይህ እውን እንዲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሌሎች የጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ የጎላ ሚና መጫወቱንም አድንቀዋል። መንግሥት ዜጎችን በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን ጥረቶች ለማሰናከል የሚንቀሳቀሱ የጸረ ሰላም ኃይሎች ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመተባበር እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ በተቀናጀ የአሰራር ሥርዓት የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት በማጽናትና የጸረ ሰላም ኃይሎችን ከንቱ ዓላማ በማምከን ያስመዘገበው ውጤት የሚያኮራ ነው ብለዋል። በመሆኑም መላው የአዲስ አበባ ፖሊስ አመራርና አባላት የጸረ ሰላም ኃይሎችን ተልዕኮ በማክሸፍ የተገኘውን ስኬት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪም ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከል እና ወንጀል ሲፈጸም ፈጣንና ውጤታማ ምላሽ በመስጠት ረገድ የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ከህብረተሰቡ እና ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል - የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
Aug 2, 2026 697
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት ከህብረተሰቡ እና ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራትን ማከናወኑን አስታወቀ። ዋና ጠቅላይ መምሪያው በ2018 ዓ.ም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የስራ ክፍሎች አመራርና እና አባላት እንዲሁም ተቋሙ ስኬታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና ምስጋና መርሃ ግብር እያካሄደ ነው። በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ባለው መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ፣ የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ሊዲያ ግርማ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ፣ የፖሊስ አመራር እና አባላትን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ጠቅላይ መምሪያው ከህዝቡ እና ሌሎች ፀጥታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራት አከናውኗል። ዓመቱ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫን ጨምሮ ትላልቅ አህጉራዊ ኹነቶች የተካሄዱበት መሆኑን አስታውሰው፤ ኹነቶቹ በስኬት እንዲካሄዱ የከተማው ፖሊስ ከተለያዩ የጸጥታ ተቋማት ጋር በጋራ በመሆን አመርቂ ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል። በማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገለግሎት ህዝቡን ተሳታፊ በማድረግ ስኬታማ ስራ መከናወኑን ገልጸው፤ በዚህም የመዲናዋን ሰላም በማጽናት ረገድም ተጠቃሽ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል። ዋና ጠቅላይ መምሪያው የፖሊስ አባላቱን ውጤታማነት ይበልጥ የሚያልቁ አሰራሮችን እየተገበረ መሆኑን አስታውቀዋል። ለፖሊስ አባላት መኖሪያ የሚሆን ባለ 15 ወለል ህንጻዎች ግንባታ መጀመሩን አስታውሰው፤ የዋና መምሪያው ቢሮ ዕድሳትም በቅርቡ ይጠናቀቃል ብለዋል። የዛሬው የእውቅናና ምስጋና መርሃ ግብር በቀጣይም የሚከወኑ ስራዎች በላቀ ተነሳሽነት እንዲሰሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
የምክክር ጉባኤው የጋራ መግባባትን የሚገነባ ለአፍሪካም ተምሳሌት የሚሆን ታሪካዊ ሂደት ነው
Aug 2, 2026 703
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ጠንካራ ሀገረ መንግሥትና የጋራ መግባባትን የሚገነባ ለአፍሪካም ጭምር ተምሳሌት የሚሆን ታሪካዊ ሂደት መሆኑን ፖለቲከኞች ገለጹ። ዋናው የምክክር ጉባኤ በ4 ሺህ የሀገር ውስጥና የውጭ ዜጎች የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች መካከል ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ፖለቲከኛው አበራ በቀለ ለኢዜአ እንዳሉት፤የምክክር ጉባኤው ለዘመናት ሲቆዩ በነበሩ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ መሠረታዊ ሀገራዊ አለመግባባቶች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተከፈተ ታሪካዊ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። በጉባኤው የሕዝብ ውክልና የተሰጣቸው ተመካካሪዎችም ለዘመናት ሲጠበቅ የነበረውን ታሪካዊ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም የጋራ መግባባትን ለመፍጠር መድረኩን ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የምክክር ሂደቱ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ችግሮቻቸውን በራሳቸው አቅምና በምክክር መፍታት እንደሚችሉ የሚያሳይ በመሆኑ ለአፍሪካም ጠቃሚ ተሞክሮና ትምህርት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያን ችግሮች በራሷ መንገድ በጋራ መግባባት መፍትሔ የምትሰጥ ሀገር ስትሆን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎቷን የምታስጠብቅ ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደሚያስችል ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና ፖለቲከኛ አብርሃም በርታ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ የምክክር ጉባኤው ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር ሰላምን፣ ብሔራዊ ደህንነትንና ልማትን ለማፋጠን ከፍተኛ ፋይዳ አለው። አሁን እየተካሄደ ያለው የምክክር ሂደት የይስሙላ ሳይሆን ለረጅም ጊዜ የቆዩ መሠረታዊ ሀገራዊ ችግሮችን በተጨባጭ ለመፍታት የታለመ መሆኑን አስረድተዋል። የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች አካታችና አሳታፊነትም ሁሉም ዜጋ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎችና ችግሮች በማንጸባረቅ የጋራ ሀገራዊ መግባባትና አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ፖለቲከኞቹ እንደገለጹት፤ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን ችግሮች በዜጎቿ ምክክርና መግባባት ለመፍታት የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል ከመሆኑም በላይ የፓን አፍሪካኒዝምን እሳቤ በተግባር የሚያንጸባርቅ ሂደት መሆኑን አመልክተዋል። ይህም አፍሪካውያን ችግሮቻቸውን በራሳቸው አቅምና ችሎታ መፍታት እንደሚችሉ ጠንካራ መልዕክት የሚያስተላልፍ መሆኑን ጠቅሰዋል። የምክክሩ ውጤትም ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለቀጣናውና ለመላው አፍሪካ በሰላም ግንባታ፣ በልማትና በጋራ መግባባት ረገድ ጠቃሚ ተሞክሮ እንደሚሆን ገልጸዋል። በተጨማሪም ልዩነቶችን በኃይል ሳይሆን በውይይትና በሃሳብ የበላይነት የመፍታት የሰላም ባህልን በማጠናከር፣ ለቀጣዩ ትውልድ ተምሳሌት የሚሆን ጠቃሚ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
ሀገራዊ ምክክር ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሀገራዊ መግባባት ወርቃማ ዕድል ነው
Aug 2, 2026 736
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 26/2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ የምክክር መድረክ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና የጋራ መግባባት ወርቃማ ዕድል መሆኑን ተመካካሪ ሌተናል ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መጀመሩ ይታወቃል። በጉባኤው ላይ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በመሳተፍ በአሁኑ ወቅት በዓበይት ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ይህ ሀገራዊ የምክክር ሂደት ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም፣ አብሮነት እና የጋራ መግባባት መረጋገጥ እጅግ ታላቅ ተስፋ የተጣለበት መድረክ ሆኗል። ተመካካሪ ሌተናል ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል፣ በምክክር ሂደቱ በከፍተኛ ደስታና አክብሮት እየተሳተፉበት እንደሚገኙ ገልጸዋል። አራት ሺህ ተመካካሪዎች ለሀገሪቱ ሰላም እና የጋራ መግባባት የሀሳብ ፊት አውራሪ ሆነው እንደሚወጡ ትልቅ እምነት እንዳላቸው አንስተዋል። በመድረኩ ተመካካሪዎች ሀሳባቸውን በግልጽ በማንጸባረቅ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው፣ ከዚህ አሳታፊ ሂደት ትልቅ ትምህርት እና ልምድ መቅሰም እንደሚቻል አስገንዝበዋል። መድረኩ የመሸናነፍ ሳይሆን ሀገራዊ መግባባት የሚገነባበት ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ይህንን ታሪካዊ የምክክር ሂደት ተስፋ የጣሉበት መሆኑን አንስተዋል። ሰላማዊ የመፍትሔ ማዕድ በሆነው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሰባስቦ መመካከር የተሻለ እና የሰለጠነ አካሄድ መሆኑንም ተናግረዋል። የየትኛውም አካባቢ ችግር የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ፣ በጋራ መግባባት እና በአብሮነት መንፈስ የጋራ መፍትሔ ማበጀት እንደሚቻልም አስረድተዋል። ይህ ሀገራዊ የምክክር ሂደት በተለይም ልሂቃን በዘመናቸው ያካበቱትን ልምድ፣ ያነበቡትን እና ያወቁትን ወደ መሬት አውርደው ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚኖራቸውን አዎንታዊ ሚና የሚያበረክቱበት ወርቃማ ዕድል ነው ብለዋል። በመሆኑም ያላቸውን ሀሳብ ሰብሰብ አድርገው ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና አብሮነት አስተማማኝ መሠረት እንዲጥሉ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።
የምክክር ጉባኤው ለኢትዮጵያ አዲስ የምክክር ልምምድን የከፈተ ታሪካዊ ዕድል ነው
Aug 2, 2026 819
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 26/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለኢትዮጵያ አዲስ የምክክር ልምምድን የከፈተ ታሪካዊ ዕድል መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የፖለቲካ ፓርቲ ተወካይ ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ በጉባኤው የግልና የቡድን ፍላጎቶችን በማጥበብ ሀገራዊ ጥቅምን በማስቀደም፣ በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ ነፃና አሳታፊ ምክክር እየተካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለኢትዮጵያ አዲስ የምክክር ልምምድን የከፈተ ታሪካዊ ዕድል መሆኑንም የፖለቲካ ፓርቲ ተወካይ ተመካካሪዎች ገልጸዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ (አብን) ተወካይና ተመካካሪ ጣሂር መሐመድ እንዳሉት፤ በምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ምክክር እየተደረገ ነው። በዋናው የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይትና ንዑሳን አጀንዳዎችም በተመካካሪዎች መካከል በነፃነትና አካታችነት እየተመከረባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን መሠረታዊና መዋቅራዊ ችግሮች በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ መግባባት በመፍጠር መፍትሔ የሚሰጥ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል። የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ትዴፓ) ሊቀመንበርና ተመካካሪ አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የመደማመጥና የመግባባት ባህልን በማጠናከር በተሻለ አሳታፊነት እየተካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ከአጀንዳ ማሰባሰብና ከተሳታፊዎች ልየታ ሂደት ጀምሮ አሳታፊነትንና አካታችነትን በተግባር በማረጋገጥ ውጤታማ ሥራ መሠራቱንም አስታውሰዋል። ከአራቱም የሀገሪቱ ማዕዘናት ሕዝብን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በዋናው የምክክር ጉባኤ ላይ ሃሳባቸውን በነፃነት በማንሸራሸርና በግልጽ ተሳትፎ ተስፋ ሰጪ ምክክር እያካሄዱ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀገራዊ ችግሮችን በሰለጠነ ምክክር ለመፍታት፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ ለመምከርና ዘላቂ የሆነ መግባባት ለመፍጠር የተገኘ ታሪካዊ ዕድል መሆኑን ጠቁመዋል። የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) አባልና የጉባኤው ተመካካሪ ሙሐሙድ መሐመድ ሀሰን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች የኢትዮጵያን ብዝኅነት፣ ሕብረ-ብሔራዊ እሴቶችና የጋራ ሀገራዊ ጥቅሞችን በሚያንጸባርቁ ሃሳቦች ላይ እንዲመክሩ ዕድል ፈጥሯል። ሀገራዊ አለመግባባቶችን በጦር መሣሪያ በታገዘ ግጭትና በኃይል ለመፍታት መሞከር ዘላቂ መፍትሔ የማያማጣና አዋጭ ያልሆነ አካሄድ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህም የጋራ ሀገርን በመገንባት አዲስ የምክክር ታሪክ እየጻፍን ነው ያሉት አቶ ሙሐሙድ፤ የጉባኤው አጀንዳዎች ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ የመግባባት ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ተመካካሪ ገነነ ገረቡ በበኩላቸው፤ በምክክር ጉባኤው አንዱ የሌላውን ሃሳብ መረዳት በሚያስችል መልኩ ማንኛውም የሕዝብ አጀንዳ በነፃነት እየተንጸባረቀ ነው ብለዋል። የምክክር ጉባኤውም ለዘመናት የቆዩ የአለመግባባቶችን ለቀጣዩ ትውልድ እንዳይተላለፉ ለማድረግ ስልጡን ምክክር እያደረግን ነው ብለዋል። በተመካካሪዎች መካከልም በአርአያነት የሚወሰድ ነፃ ምክክር እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
ማህበራዊ
የተጠናቀቀው በጀት ዓመት አዲስ አበባ የዜጎችን ማህበራዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ እመርታዊ ውጤቶችን ያስመዘገበችበት ነው
Aug 4, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት አዲስ አበባ የዜጎችን ማህበራዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ እመርታዊ ውጤቶችን ያስመዘገበችበት ዓመት መሆኑ ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ልማት ክላስተር አፈጻጸምና በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊና የማህበራዊ ልማት ክላስተር አስተባባሪ ተወካይ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ እንዳሉት፤ ክላስተሩ በ2018 በጀት ዓመት በቅንጅት የተመሩ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን አከናውኗል። በአንድ ተቋም ብቻ ተጀምረው ሊጠናቀቁ የማይችሉና የሌሎች ተቋማትን ትብብር የሚሹ ሥራዎች በጋራ ታቅደው፣ በጋራ ተገምግመው በውጤታማነት መከናወናቸውንም አስታውቀዋል። በዚሁ መሠረት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በጤና፣ በትምህርትና በሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ተግባራት በቅንጅት በውጤታማነት መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ይህ የቅንጅት አሠራር ለሁሉም ተቋማት አቅም የሚፈጥርና መልካም ተሞክሮ በመሆኑ፣ በቀጣይም በሁሉም ዘርፎች ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ፤ በትምህርት ዘመኑ የተመዘገቡ ስኬቶች እንዲሳኩ የማህበራዊ ልማት ክላስተሩ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ገልጸዋል። ክላስተሩ ከተማሪዎች ጤና፣ ምገባ፣ ትምህርትና ሥልጠና ጥራትና ቁጥጥር ጋር ተያይዘው የሚከናወኑ ተግባራትን በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመዋል። በዚህም በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በሁሉም የትምህርት ተቋማት የተረጋጋ፣ ሰላማዊና ምቹ የመማርና የማስተማር ሂደት እንዲኖር ማስቻሉን ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የተቋማት ክትትል ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሞላ ንጉሥ በበኩላቸው፣ በበጀት ዓመቱ በማክበራዊ ዘርፍ እመርታዊ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። በ2019 በጀት ዓመትም የተመዘገቡ እመርታዊ ውጤቶችን በማስቀጠል የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የተቋማቱ የቅንጅት አሠራር በቀጣይም በተጠናከረ መልኩ በመቀጠል የከተማዋን ማህበራዊ አገልግሎቶች የበለጠ ውጤታማና ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ገልጸዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ውሃ ወለድ በሽታዎችን ለመከላከል በተከናወኑ የተቀናጁ የመከላከልና የመቆጣጠር ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል
Aug 4, 2026 109
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦በሀገር አቀፍ ደረጃ ውሃ ወለድ በሽታዎችን ለመከላከል በተከናወኑ የተቀናጁ የመከላከልና የመቆጣጠር ሥራዎች ውጤት መገኘቱን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብሔራዊ ኮሌራን የማጥፋት ዕቅድና በተከናወኑ ተግባራት ላይ ያተኮረ የሦስት ቀናት የምክክር መድረክ ማካሄድ ጀምሯል። በመድረኩ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መልካሙ አብቴ እንደገለጹት፤ በክረምት ወቅት የሚከሰቱ የውኃ ወለድ በሽታዎችን ለመከላከል ሕብረተሰቡ የታከሙ ውኃዎችን መጠቀምና ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባል፡፡ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የመከላከል ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የተጠቆመ ሲሆን፤ ሕብረተሰቡ አጠራጣሪ ነገር ሲገጥመው በ 8335 ነፃ የስልክ መስመር በመደወል መረጃ ማግኘት እንደሚችል አብራርተዋል፡፡ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ዝግጁ መሆናቸውንና ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ህክምና ማግኘት እንደሚችልም አስረድተው፤ ከዚህ ቀደም የኮሌራ በሽታን ለመከላከል በተከናወኑ የተቀናጁ የመከላከልና የመቆጣጠር ሥራዎች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። በንጽህና፣ በክትባት እንዲሁም በቅድመ-መከላከል ዘርፍ የተከናወኑት ስኬታማ ተግባራት ኮሌራን ለማጥፋት ያስቻሉ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህንኑ ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል የተቀናጀ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቀረጸው ኮሌራን የማጥፋት ስትራቴጂ ለሌሎች ሀገራት በምሳሌነት የሚጠቀስና ውጤታማ በሆነ መንገድ እየተተገበረ የሚገኝ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ በዚሁ ዘርፍ ለአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን ተግባር ማከናወኗንና በድንበር አካባቢዎችም ከጎረቤት ሀገራት ጋር በቅንጅት እየተሠራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ከአጋር ድርጅቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረገው ይህ የምክክር መድረክም በሽታውን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት የሚደረገውን ጥረት ያጠናክረዋል ብለዋል። በኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር፣ ምላሽና መልሶ ማገገም ዳይሬክተር አቶ መደኃንዬ ሀብተጽዮን በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል የሰው ኃይልና የላቦራቶሪ አቅም መገንባቱን ገልጸዋል። ይህም ፈጣን የልየታ ሥራዎችን ለማከናወንና አፋጣኝ ምላሾችን ለመስጠት ማስቻሉን አብራርተዋል። በመድረኩ የተገኙት በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የድንገተኛ አደጋዎች ባለሙያ ዶክተር ኢኖሰንት ኮማኬች በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ ኮሌራ የሕብረተሰብ ጤና ሥጋት እንዳይሆን ያከናወነችው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ የሚያደርገውን አጋርነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በድሬዳዋ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን ለማሳደግ የተለያዩ መርሐ ግብሮች ተግባራዊ እየተደረጉ ነው
Aug 4, 2026 101
ድሬደዋ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን ለማሳደግ የተለያዩ መርሐ ግብሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን የአስተዳደሩ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ባለፉት ሁለት ዓመታት የገነባቸውን 367 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዛሬ በዕጣ ለባለዕድለኞቹ አስተላልፏል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ኢማጅ አብደላ በከተማው እየጨመረ ለመጣው የቤት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት ቢሮው እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ገንብቶ ለነዋሪዎች በፍትሃዊነት ተደራሽ የማድረጉ ተግባርም ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለትም የ367 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ በዲጂታል አሠራር እንዲወጣ ተደርጎ ለቆጣቢዎች መተላለፉን ተናግረዋል። የአስተዳደሩ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከድር አልይ በበኩላቸው አስተዳደሩ ባለሀብቶችን እና ሕብረተሰቡን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በማስተባበር አዳዲስና ነባር ቤቶችን የማደስና የመገንባት ተግባር ማከናወኑን ጠቅሰዋል። ለመምህራን የቤት ግንባታ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠትም ከባንክ ጋር የማስተሳሰር ስራ መሠራቱን ገልጸው፤ የቤት ልማትን በማጠናከርም በ10/90 እና በ20/80 አሠራር በፍጥነትና ጥራት ለማስተናገድ በትጋት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ከቤት ዕድለኞች መካከል የ08 ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሺባን አሜ እና የ04 ቀበሌ ነዋሪ አቶ ገነነ ኃይሉ አስተዳደሩ የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ የሄደበት ርቀት የሕዝብን ጥያቄ የመለሰ መሆኑን ተናግረዋል።
በዞኑ የፍትህ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የማስደገፍና የማዘመን ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Aug 4, 2026 131
አዳማ ፤ሐምሌ 28/2018(ኢዜአ)፡-በምስራቅ ሸዋ ዞን የህግ የበላይነትን ለማስከበር የፍትህ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የማስደገፍና የማዘመን ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ አስገነዘቡ። የምስራቅ ሸዋ ዞን ፍርድ ቤቶችና የፍትህ አካላት የሪፎርም ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ 7ኛው የምክክር ጉባኤ በአዳማ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የምስራቅ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ በዞኑ የፍትህ አገልግሎትን ፈጣን፣ ጥራት ያለውና ዘመናዊ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸዉን ገልፀዋል። በተለይም በፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበረው የህዝብ ቅሬታ እየተቀረፈ መምጣቱን ያመለከቱት አቶ አባቡ፤ የተካሄደው የፍትህ ማሻሻያ ሪፎርም የህብረተሰቡን የመንግስት አገልግሎት እምነት ያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። በዘርፉ አበረታች ውጤቶች ቢመዘገቡም የተገልጋዮችን እንግልትና ምልልስ ማስቀረት፣ የሐሰት ምስክርነትን ማጥፋት እንዲሁም የመልካም አስተዳደርና የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በመሆኑም በዞኑ ጥራት ያለው፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት ለመስጠት በቴክኖሎጂ የተደገፈ የዲጂታላይዜሽን ስራ በወረዳ ፍርድ ቤቶች በተጠናከረ መልኩ ስራ ላይ ሊውል እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ዘውዴ ፍቃዱ በበኩላቸው፤ የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ጥራቱን ለማስጠበቅ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ፈጣንና ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግና የተገልጋይን እርካታ ለማረጋገጥ በወረዳና በዞን ፍርድ ቤቶች የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በስፋት ስራ ላይ መዋሉንም ጨምረው ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ቀርበው ከነበሩት ከ23 ሺህ በላይ የክስ መዝገቦች ውስጥ ከ22 ሺህ 900 በላይ የሚሆኑት እልባት ማግኘታቸውን እንደ አብነት ገልጸዋል። በቀጣይነት የፍትህ ዘርፉን ጥራት ለማረጋገጥ በተለይም በበየነ-መረብ አማካኝነት ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው ክርክር፣ ምላሽና ውሳኔ እንዲያገኙ መደረጉን ያመለከቱት ፕሬዝዳንቱ፤ በ2019 ዓ.ም የዞኑን የፍትህ አገልግሎት ከወረቀት ንክኪ ነፃ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተያዘው የበጀት ዓመት አገልግሎቱን ከወረቀት ንክኪ ነፃ ለማድረግ እንዲቻል 98 ሺህ መዝገቦች ወደ ሶፍት ኮፒ የተቀየሩ ሲሆን፤ ለዲጂታል አገልግሎትም ዝግጁ መደረጋቸውን ተናግረዋል። በጉባዔው ላይ በየደረጃው ካሉ የዞኑ ፍርድ ቤቶች፣ ዐቃቤ ህጎች፣ የፀጥታ አካላትና አመራሮች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎችና ሃደ ሲንቄዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ኢኮኖሚ
በሀረሪ ክልል ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን ለማጎልበት በትኩረት ይሰራል
Aug 4, 2026 104
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 28/2018(ኢዜአ) ፦ በሀረሪ ክልል ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን በማጎልበትና የስራ ፈላጊዎችን የስራ ባህል ማሳደግ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ የስራ እድል ፈጠራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር ገለጹ። የክልሉ የስራ እድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 በጀት አመት የስራ እድል ፈጠራ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት አመት እቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል። ሰብሳቢዋ በመድረኩ ላይ በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመፍታትና አዳዲስ ቋሚ የስራ እድሎች ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን በማጎልበት እንዲሁም የስራ ፈላጊዎችን የስራ ባህልና ግንዛቤ ማስፋት ከቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መካከል መሆኑንም ወይዘሮ ሮዛ ተናግረዋል። በተለይም ገበያ ላይ ተፈላጊ የሆኑ የክህሎት ስልጠናዎችን ከመስጠት ጀምሮ የዜጎችን የስራ ባህል በማሳደግ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራም ጠቁመዋል። በ2019 የበጀት አመት እቅድን ለማሳካት በሚከወኑ ስራዎች የሚገጥሙ ውስንነቶችን ለመቅረፍ በትኩረት መንቀሳቀስ እንደሚገባ ገልጸው የሚመለከታቸው አካላትም በቅንጅት መስራት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል። በዚህም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ለስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ ከእቅድ ጀምሮ እስከ አፈጻጸሙ ድረስ ቅድሚያ በመስጠት በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ወይዘሮ ሮዛ ተናግረዋል፡፡ የክልሉ የኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢስማኢል ዩሱፍ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳመላከቱት በስራ እድል ፈጠራና ስልጠና ዙሪያ ከልማት አጋር አካላት፣ ከመንግስትና ከግል ሴክተሮች ጋር በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል። በተጠናቀቀው የበጀት አመትም 11 ሺህ ቋሚ የስራ እድሎችን በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎትና በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት በገጠርና በከተማ ለሚገኙ ዜጎች መመቻቸቱ ተገልጿል። በተፈጠረው የስራ እድልም በዋናነት ወጣቶች፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና ከስደት ተመላሽ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማኅበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው
Aug 4, 2026 111
ቡታጅራ ፤ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለፀ። በቢሮው "አንድነት ለፅዳት፣ ትጋት ለአገልግሎት፣ ውሳኔ ለልማት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የሴክተሩ የምክክር መድረክ በቡታጅራ ከተማ ተካሄዷል። በወቅቱም የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል እንዳሉት በክልሉ የማኅበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው። በዚህም ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው በኮሪደር ልማትና የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን ረገድ የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። የስልጤ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱልሰመድ አብደላ በበኩላቸው በዞኑ ዘመናዊና የተሳለጠ አገልግሎቶችን በመስጠት የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኮሪደር ልማት ሥራ ከተሞችን ምቹ፣ ፅዱና ተመራጭ ከማድረግ ባለፈ የገጠር ቀበሌዎች ለኑሮ የተመቹና የወደፊቱን የከተሞች ዕድገት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲለሙ እየተደረገ ነው ብለዋል። ለዚህም ስኬት በዞኑ በሚገኙ 3 ወረዳዎች የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘዬ የሚቀይሩ 24 ቤቶች መገንባታቸውንና በዕቅድ የተያዙትን ቀሪ ቤቶች ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በከተማው በመሬት ዘርፍ በሚሰጡ አገልግሎቶች የሚነሱ የማኅበረሰቡን ቅሬታዎች ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ያሉት ደግሞ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ ናቸው። በተለይም 45 የሚጠጉ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች በመሶብ የአንድ ማዕከል እንዲሰጡ መደረጉ ለውጥ እንዳመጣም ጠቁመዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የክልል፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
በክልሉ የከተሞችን እድገትና የገጠር የልማት ሽግግር ዘላቂነት ታሳቢ ያደረገ ፕላን በማዘጋጀት እየተተገበረ ነው
Aug 4, 2026 122
ባህር ዳር፤ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የወቅቱን የከተሞችን እድገትና የገጠር የልማት ሽግግር ዘላቂነት ታሳቢ ያደረገ ፕላን በማዘጋጀት እየተተገበረ እንደሚገኝ የክልሉ ፕላን ኢንስቲትዩት ገለጸ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ምትኩ ዓለማየሁ (ዶ/ር) ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳሉት፤ በክልሉ ከተሞችና የገጠር ቀበሌዎች መጪውን እድገትና የሕዝብ አኗኗር መሠረት ተደርጎ እየተሠራ ነው። ከተሞች ካላቸው ፈጣን እድገት ጋር ተያይዞ ዘላቂነት ያለው የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የመኖሪያ አካባቢዎች፣ ማህበራዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትንና ሌሎችንም ሁኔታዎች ባሟላ መንገድ መጪውን ጊዜ ታሳቢ በማድረግ በፕላን እንዲመሩ እየተደረገ ይገኛል። እንዲሁም የገጠር ሽግግርን የተሳካ ለማድረግ የገጠር ቀበሌ ማዕከላት በፕላን ላይ መሠረት አድርገው እንዲቋቋሙ በቅንጅት እየተሠራ እንደሆነም አንስተዋል። በተለይም የኮሪደር ልማት ኢኒሼቲቭ፣ ከተሞችና የገጠር አካባቢዎች በዘላቂ ፕላን እንዲመሩ አስገዳጅ ከመሆኑም በላይ ለዘላቂ እድገት መልካም ሆኖ መገኘቱን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ በ2018 በጀት ዓመት ተቋማዊ ሪፎርም ከማድረግ ባሻገር ለአሠራር የሚያግዙ የሕግ ማሻሻያዎችን የማድረግ ሥራ ተሠርቷል ብለዋል። እንዲሁም 137 የተለያየ ዓይነት ፕላን በማዘጋጀት ወደ ትግበራ እንዲገባ መደረጉን ጠቅሰው፤ ከእነዚሁ ውስጥ 37 የሚሆኑት የገጠር ቀበሌ ማዕከላት ፕላኖች መሆናቸውን ገልጸዋል። በፕላን ዝግጅቱ ከ14 ሺህ በላይ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ማሳተፍ መቻሉን ጠቅሰው፤ የፕላን ትግበራ፣ ክትትልና ቁጥጥር ሥራ መካሄዱንም አብራርተዋል። ኢንስቲትዩቱ በ2019 በጀት ዓመትም 187 የተለያየ ዓይነት ፕላን ለማዘጋጀት አቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቅሰዋል። የፕላን ዝግጅቱ የክልሉን የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማትና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ መሠረት በማድረግ እየተተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከሚዘጋጀው ፕላን ውስጥም 130 ያህሉ የገጠር ቀበሌ ማዕከላት መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይህም መንግሥት ለገጠር ሽግግር የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የሚሠራ ነው ብለዋል። የገጠር ማዕከላቱ የመኖሪያ አካባቢዎችን፣ መሠረተ ልማትን፣ የገበያ ቦታዎችን፣ ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትንና የአርሶ አደሩን የግብርና ሥራ በሚያሳልጥ አግባብ የሚሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተዘጋጅተው የሚቀርቡ ፕላኖች ወደ ትግበራ ሲገቡ በየደረጃው የሚገኝ አመራርና ባለሙያ ሕብረተሰቡን በማሳተፍ መተግበር እንዳለበትም ዋና ዳይሬክተሩ አሳስበዋል።
ታዋቂው ሲ ኤን ኤን ቴሌቪዥን ጣቢያ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ
Aug 4, 2026 285
ታዋቂው የሲኤንኤን የቴሌቪዥን ጣቢያ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ ባለፈ የቀጣናው ሀገራትን የኢነርጂ ተጠቃሚ ያደረገ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን በዘገባው አስቃኝቷል። ግድቡ በሚሊየኖች ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ብርሃን ያደረሰ መሆኑንም አመላክቷል። በሲኤንኤን ዘጋቢ የሆነችው ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ባሰናዳችው ዘገባ÷ ወደ ጉባ በማቅናት የግድቡን እውነታ አስቃኝታለች። በዚህም በሺዎች የሚቆጠሩ በርካታ የምህንድስና ባለሙያዎች እና የግንባታ ባለሙያዎች ሸለቋማ የሆነውን አካባቢ ወደ አፍሪካ ግዙፍ ግድብ መቀየራቸውን ገልጻለች። ግድቡ የምህንድስና ልህቀት የታየበት ነውም ብላለች። ከ14 ዓመታት የግንባታ ቆይታ በኋላ ህዳሴ ግድብ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 መመረቁን ገልጻለች። ግድቡ በኢትዮጵያውያን ድጋፍ፣ የመንግስት ፋይናንስ፣ ቦንዶች እና የተለያዩ የሀገር ውስጥ የፋይናንስ አማራጮች በኢትዮጵያዊያን አቅም መገንባቱን ተናግራለች። ይህ ግዙፍ ግድብ ለሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያውን ብርሃን የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን በጎረቤት ሀገራትም የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት እንዲደርስ የሚያደርግ ነው። በዚህም ግድቡ ከኢትዮጵያ ባለፈ የቀጣናዊ ኃይል ትስስር ማእከል እንዲሁም የቱሪስት መዳረሻ በመሆን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግራለች። ሲኤን ኤን በዘገባው ላይ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮን በማቅረብ ኢትዮጵያ የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት በማይጎዳ መልኩ ግድቡን እየተጠቀመች መሆኑን አመላክቷል። ግብፅ በግድቡ ምክንያት የሚደርሳት ውሃ ቀንሷል በሚል የምታቀርበው ክስ መሰረተ ቢስ መሆኑንም ኢንጂነር ክፍሌ አስረድተዋል፡፡ አሁን ላይ በሕዳሴ ግድቡ የሚገኙ 13 ተርባይኖች በሚያመነጩት ሀይል 6 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ግድቡ ከኢትዮጵያ አልፎ ሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ ሀይል ተደራሽ ማድረግ መቻሉን፣ በቀጣይ ደግሞ ለሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳን ሀይል ለመሸጥ ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል፡፡ በተጨማሪም በሕዳሴ ግድቡ በተፈጠረው ንጋት ኃይቅ ላይ የተፈጠሩት ደሴቶች ለቱሪስት መስህብነት ትልቅ አቅም መሆናቸውን በማንሳት ፤ በቀጣይም ለቱሪስት መዳረሻነት የሚያገለግሉ መሰረተ ልማቶች እንደሚገነቡ ጠቁመዋል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Aug 4, 2026 32
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት ዛሬ የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረውን ፋይዳቨርስን በይፋ ሥራ አስጀምረናል ብለዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ወደ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎችን በመመዝገብ፣ ከ160 ሚሊዮን በላይ የማረጋገጫ አገልግሎቶችን በመስጠትና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ የዲጂታል ኢኮኖሚያችን የጀርባ አጥንት መሆኑን አስመስክሯል ነው ያሉት። ዛሬ ደግሞ ይህ ስኬታችን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ተሸጋግሮ፣ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር ፋይዳቨርስ በሚል ስያሜ ራሱን የቻለ የመንግስት የልማት ድርጅት በመሆን ወደ ስራ ገብቷል ብለዋል። ይህ ውሳኔ ዲጂታል ማንነት ልክ እንደ መንገድ፣ ኃይል እና ቴሌኮሙኒኬሽን ሁሉ ለሀገራችን ተወዳዳሪነትና ዘላቂ እድገት ወሳኝ የሆነ ስትራቴጂካዊ ሀገራዊ መሰረተ ልማት መሆኑን ማረጋገጫችን ነው ሲሉ ገልጸዋል። ከሀገር አልፎ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሰረት ለቀጣናው እና ለአፍሪካ አህጉር ልምድና አቅም በማጋራት የአፍሪካ የዲጂታል ሽግግር መሪ እንድንሆን ያስችለናል። የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዟችን ስኬት የሚለካው በደረስንባቸው ቴክኖሎጂዎች ሳይሆን፣ ሕዝባችን እነዚህን ውጤቶች የራሱ አድርጎ ሲጠቀምባቸው እና ህይወቱ ሲለወጥ ነው። የቴክኖሎጂ አቅርቦታችንን ጥራት በመጠበቅ፣ የዳታ ደህንነታችንን በማረጋገጥ እና የዜጎቻችንን ዲጂታል ግንዛቤ በማሳደግ የያዝነውን አቅጣጫ በበለጠ ቁርጠኝነት እንቀጥላለን ብለዋል።
የመደመር መንግሥት የዲጂታል መሠረተ ልማት እመርታ የዜጎችን ተጠቃሚነት እያሳለጠ ነው - ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)
Aug 4, 2026 35
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግሥት በዲጂታል መሠረተ ልማት ያስመዘገበው እመርታ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳለጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ፋይዳ) በመንግሥት የልማት ድርጅትነት እንደገና ተደራጅቶ "ፋይዳ ቨርስ ዲጂታል ሶሉሽንስ ኢንተርፕራይዝ" በሚል ስያሜ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሥር ተካቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው የ"ፋይዳ ቨርስ" ይፋዊ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ፋይዳ ቨርስ የኢትዮጵያን የዲጂታል ዘመን ጥንካሬ፣ ዘላቂነትና በዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ያጎለብታል ብለዋል። ባለፉት ስምንት ዓመታት የመደመር መንግሥት የቴሌኮሙኒኬሽን መሠረተ ልማትን በማጠናከር በድምፅና በኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን ገልጸዋል። የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎቶችም የመንግሥትን አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት እያሳደጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። የፋይዳ አገልግሎት በአፍሪካ ከፍጥነት የዲጂታል ማንነት ሥርዓቶች አንዱ እየሆነ ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ፋይዳ ቨርስ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስን መቀላቀሉም ተቋማዊ ጥንካሬን ይፈጥራል ብለዋል። የኢትዮጵያ የሕዝብ መሠረተ ልማት የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅምና ልምድም ደኅንነቱ የተጠበቀ የዲጂታል ማንነት ሥርዓት በመገንባት በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት እየሳበ መሆኑን አንስተዋል። የፋይዳ ቨርስ ዲጂታል ሶሉሽንስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዮዳሄ አርዓያሥላሴ በበኩላቸው፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ የዜጎችን ማንነት በዲጂታል መንገድ የመመዝገብና የማረጋገጥ ሰፊ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም በአዲስ መልክ "ፋይዳ ቨርስ ዲጂታል ሶሉሽንስ" በሚል ወደ የመንግሥት የልማት ድርጅት ማደጉም የዲጂታል ውጤታማነትን የበለጠ ለማጎልበት የተወሰደ ስትራቴጂያዊ እርምጃ መሆኑን አስረድተዋል። ተቋማዊ ሽግግሩም በራስ አቅም የቴክኖሎጂ ፈጠራንና ዘላቂ የፋይናንስ መሠረትን በማጣመር ወደ ተሻለ የዲጂታል አገልግሎትና የንግድ ሥርዓት ለመሸጋገር የተዘጋጀ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል። በዲጂታል ማንነት መሠረተ ልማት የተፈጠረው አቅም ለፈጠራ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለፋይናንስ አካታችነትና ለዘመናዊ የመንግሥት አገልግሎቶች ጠንካራ መሠረት እንደሚሆንም አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ የዲጂታል ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Aug 4, 2026 51
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዲጂታል ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው የ"ፋይዳቨርስ" ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፤ የ"ፋይዳቨርስ" ሥራ መጀመር ኢትዮጵያ ለዲጂታል ሉዓላዊነቷ የሰጠችውን ከፍተኛ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራሙ ለሀገሪቱ የዲጂታል ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ሆኖ መገንባቱን ጠቅሰው፤ እስካሁን ወደ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ይህም ከ13 ሚሊዮን በላይ የብሔራዊ መታወቂያ ካርዶች ታትመው መሰራጨታቸው፣ ከ160 ሚሊዮን በላይ የማንነት ማረጋገጫ አገልግሎቶች መሰጠታቸውና በ13 ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች የዲጂታል ማንነት መሠረተ ልማት መዘርጋቱን አስረድተዋል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራሙ እንደ መንግሥት የልማት ድርጅት በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር "ፋይዳቨርስ" በሚል ስያሜ እንደገና መደራጀቱን ገልጸዋል። ፕሮግራሙም የኢትዮጵያ ይፋዊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ማዕከል ሆኖ እንደሚያገለግል ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ እ.አ.አ. በ2030 የኢትዮጵያን ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በ6 በመቶ እንዲያሳድግና በቢሊዮኖች ዶላር የሚለካ ቀጥተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዲያመጣ ትልቅ ተስፋ እንደተጣለበት ገልጸዋል። አገልግሎቱ ከነባሩ Fayda ID መተግበሪያ በተሻሻለ መልኩ በFaydaPass አፕሊኬሽን እና በሌሎች ዘመናዊ ዲጂታል ምርቶች የቀረበ በመሆኑ የአገልግሎቱን ተደራሽነትና የመፍትሔ አቅም በእጅጉ እንደሚያሳድግ አስገንዝበዋል። ዳታ በዘመናችን የኢኮኖሚና የሉዓላዊነት ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ፣ የሀገራዊ መረጃዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ ዘመናዊ የሳይበር ደህንነት ቴክኖሎጂዎችን እና ጠንካራ የዳታ አስተዳደር ፖሊሲዎችን በተከታታይ መተግበር እንደሚገባ አክለዋል። ቴክኖሎጂ በገጠርና በከተማ የሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያገናኝ፣ የአገልግሎት ተደራሽነትን የሚያሰፋና ድህነትን ለመቀነስ የሚያግዝ መሆን እንዳለበት አስረድተዋል። የዜጎችን የዲጂታል ግንዛቤ ማሳደግ የስትራቴጂው ዋነኛ አካል መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ መሠረት የዲጂታል መሠረተ ልማት ልምድን ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማጋራት የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ይህም ለአህጉራዊ ትብብርና የዲጂታል ዲፕሎማሲ ጠንካራ መሠረት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እንደ ሀገሪቱ የሉዓላዊ ሀብት ፈንድ ሀገራዊ ሀብቶችን በብቃት ለማስተዳደር እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። "ፋይዳቨርስ" ወደዚህ ቤተሰብ መቀላቀሉም ዲጂታል ማንነት ልክ እንደ መንገድ፣ ኃይልና ቴሌኮሙኒኬሽን ወሳኝ ስትራቴጂካዊ መሠረተ ልማት መሆኑን የሚያረጋግጥ ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል። ይህ ስኬት እውን እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ የተቋሙ አመራሮች፣ ሠራተኞችና የልማት አጋሮች ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይልን ለኤሌክትሪክ ማመንጨት ለመጠቀም በያዘችው ዕቅድ መሠረት ዓለም አቀፍ የቁጥጥርና የሕግ ማዕቀፏን እያጠናከረች ነው
Aug 4, 2026 339
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይልን ለኤሌክትሪክ ማመንጨት ለመጠቀም በያዘችው ዕቅድ መሠረት ዓለም አቀፍ የቁጥጥርና የሕግ ማዕቀፏን እያጠናከረች መሆኗን የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለሥልጣን ገለጸ። የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለሥልጣን በኒውክሌር ጣቢያዎች ላይ ባዘጋጀው ረቂቅ የቁጥጥር ደንብ ዙሪያ ከመንግሥት ተቋማት፣ ከሙያ ማኅበራትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው፡፡ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሰሎሞን ጌታቸው (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂን ለሰላማዊ ዓላማና ለኤሌክትሪክ ማመንጨት የመጠቀም ፍላጎቷን ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ በይፋ ካሳወቀች በኋላ፣ የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማጠናከር ሰፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በዚህም ሂደት የሰው ኃይል አቅም ግንባታ፣ የሕግና የቁጥጥር ማዕቀፎች ዝግጅት፣ የፈቃድ አሰጣጥ እንዲሁም የኢንስፔክሽንና የሕግ ማስከበር ሥርዓቶች በዓለም አቀፍ መስፈርቶች መሠረት እየተገነቡ ይገኛሉ ብለዋል። የኒውክሌር ጣቢያዎች ቦታ መረጣ፣ የአካባቢና የሕዝብ ደኅንነት ጥበቃ፣ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ አደጋዎች መከላከል እንዲሁም የአደጋ ጊዜ ምላሽ አሰጣጥ መስፈርቶች በረቂቅ ደንቡ ውስጥ መካተታቸውን ገልጸዋል። ባለሥልጣኑ ከአሜሪካ የኒውክሌር ቁጥጥር ኮሚሽን (USNRC)፣ ከሩሲያው የቁጥጥር ተቋም (Rostechnadzor) እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር የአቅም ግንባታና የሙያ ትብብር እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በውይይቱ ከባለድርሻ አካላት የሚሰበሰቡ ግብዓቶች ረቂቅ የቁጥጥር ደንቡን በማሻሻልና ለማጽደቅ መሠረት እንደሚሆኑም ገልጸዋል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ወደ አሜሪካ አመራ
Aug 3, 2026 301
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ)፦ በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት፣ ዩጂን ከተማ በሚካሄደው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ምሽቱን ወደ ውድድሩ ስፍራ አቅንቷል። ሻምፒዮናው በዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ታሪካዊ መድረክ በሆነው በሄይዋርድ ፊልድ ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን፣ ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ ወጣት አትሌቶች ይሳተፋሉ። ሻምፒዮናው ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። በዘንድሮው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር (በሁለቱም ፆታዎች)፣ 3000 ሜትር መሰናክል (በሴቶች)፣ 400 ሜትር (በሴቶች) እንዲሁም በርምጃ ውድድር (በሁለቱም ፆታዎች) ትሳተፋለች። የኢትዮጵያ አትሌቶች በሻምፒዮናው ላይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅታቸውን አድርገዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣ የፌዴሬሽኑ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አመንሲሳ ከበደ (ዶ/ር) እና የፌዴሬሽኑ የስልጠና፣ ጥናትና ምርምር ዳይሬክተር አሰፋ በቀለ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በመገኘት ልዑክ ቡድኑን መሸኘታቸውን የፌዴሬሽኑ መረጃ ያመለክታል። በዘንድሮው ሻምፒዮና ላይ ከ147 ሀገራት የተውጣጡ ከ1800 በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ። እ.አ.አ በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከዓለም ሁለተኛ በመሆን ማጠናቀቋ የሚታወስ ነው።
ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በስፖርት መሰረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ መስራት ይገባል
Jul 26, 2026 582
ሀዋሳ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እግር ኳስ ተወዳዳሪና ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በስፖርት መሠረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ የሚሰሩ ስራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተጠቆመ። እ.አ.አ. በ1957 የተመሰረተው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መስራች ከነበሩ ሀገራት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እግር ኳስ ዕድገት ትልቅ አሻራ አሳርፋለች። የአፍሪካ እግር ኳስ በዓለም መድረክ የሚገባውን ቦታ እንዲይዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉት የካፍ ፕሬዝዳንት የነበሩት የይድነቃቸው ተሰማ ሀገር ኢትዮጵያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የእግር ኳስ አፍቃሪያን ያሉባትም ናት። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እግር ኳስ ዕድገት ያኖረችውን አሻራና የቀደመ ገናና ታሪክ በማንሳት የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ጥያቄ ማቅረቧም ይታወቃል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ዋና አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ እና የክለቡ ተጫዋች ሁሴን ጠሃ፤ በኢትዮጵያ ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በመሰረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ በእግር ኳሱ የላቀ ችሎታ ያላቸው ተጫዋቾች እንዳሏት አንስተው ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት ዕድሎችን ለመጠቀም ብዙ ልንሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። የ2018ቱ የሲቢኢ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው ቡድን አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ እንደገለጸው፤ ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት ሌላው ዓለም የሚሰራውን መስራት መቻል አለብን ። የስፖርት መሰረተ ልማትና የታዳጊ ስልጠና ማዕከላትን ማጠናከር፤ የምልመላ ስርዓትና የውድድር ዕድሎችን ማስፋት ቀዳሚዎች መሆናቸውን አንስቷል። ዕምቅ ችሎታ ያላቸው ተጫዋቾች የሚፈሩባቸው ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የሚደረጉ ስልጠናዎችና ውድድሮች ላይ ማተኮር እንደሚገባም አክሏል። አሰልጣኞችን ልምድ ባላቸው ሀገራት ማስተማር፣ ወጥ የሆነ የስልጠና ማኑዋል ማዘጋጀትና ሳይንሳዊ የሆነ የምልመላ ስርዓት መዘርጋት ሌላው ሊተኮርበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አንስቷል። መንግስት የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ጥያቄ ማቅረቡ በስፖርቱ ዘርፍ ከፍተኛ የሆነ መነሳሳትን እንደሚፈጥር የጠቀሰው አሰልጣኝ ያሬድ ዕድሉን መጠቀም ይገባናል ሲል ገልጿል። ለዋናው ብሔራዊ ቡድን የመጫወት ህልም ይዞ እየሰራ ያለው የክለቡ ከ20 ዓመት በታች የግራ መስመር አጥቂ ሁሴን ጠሃ በበኩሉ፤ ተፎካካሪ ብሔራዊ ቡድን ለመፍጠር ታዳጊዎችና የስልጠና ሜዳዎች ሊጠናከሩ ይገባል ነው ያለው።
የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
Jul 24, 2026 654
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን የርገን ክሎፕን የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የ59 ዓመቱ ጀርመናዊ የአራት ዓመት ውል የተፈራረሙ ሲሆን ስምምነቱ አሰልጣኙን እስከ 2030 የዓለም ዋንጫ መጨረሻ ድረስ የሚያቆያቸው ነው። ክሎፕ በቦታው የተኩት በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ጀርመን በ32ቱ ዙር በፓራጓይ ተሸንፋ ከውድድሩ ውጪ ከሆነች በኋላ ከኃላፊነታቸው የለቀቁትን ጁሊያን ናጌልስማንን በመተካት ነው። ከሊቨርፑል የዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ የሬድ ቡል ሳልስበርግ የዓለም እግር ኳስ ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት ክሎፕ፣ የጀርመን እግር ኳስን እንደገና ወደ ቀደመ ገናናነቱ የመመለስ ትልቅ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ክሎፕ ከጀርመን ብሔራዊ ቡድን ጋር የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም. በዩኤፋ ኔሽንስ ሊግ (Uefa Nations League) ከኔዘርላንድስ ጋር ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በአንድ ጀምበር የተጻፈ ታሪክ፦ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬት
Aug 4, 2026 174
የአንድ ሀገር የታላቅነት መለኪያዎች አንዱ የታቀዱ አገራዊ ግቦችን ወደ ተጨባጭ ተግባር የመለወጥ ብቃት ነው። ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅዳ፣ 805.3 ሚሊዮን በመትከል ያስመዘገበችው አዲስ ታሪካዊ ስኬት፣ አገሪቱ ያቀደችውን በተግባር ማሳየት የምትችልና ትልልቅ ህልሞችን የመተርጎም አቅም ያላት ታላቅ አገር መሆኗን ለመላው ዓለም አስመስክሯል። በአንድ ቀን ውስጥ የተከናወነው ይህ ግዙፍ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በርካታ ጥልቅ ትርጉሞችን አዝሏል። በአንድ ጀምበር ከ805.3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ከፍተኛ የሎጂስቲክስ፣ የቅድመ-ዝግጅትና የህዝብ ንቅናቄ ሥራን ይጠይቃል። ይህ ስኬት አገሪቱ ማንኛውንም ታላቅ አገራዊ እቅድ እስከ መጨረሻው የትግበራ ምዕራፍ ድረስ በብቃት የመምራትና የማስተባበር ተቋማዊና ህዝባዊ አቅም እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች በዕድሜ፣ በጾታ ወይም በሌሎች ልዩነቶች ሳይወሰኑ በአንድ ቀን ለአንድ ተመሳሳይ አገራዊ ዓላማ መቆማቸው፣ ኢትዮጵያውያን ለጋራ እድገታቸውና ለወደፊት ተስፋቸው ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትና አንድነት ያሳያል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት ዋና ስጋት በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ እርምጃ ለችግሩ መፍትሔ በመስጠት ረገድ ዓለም አቀፍ መሪነቷን ያስመሰከረችበት አጋጣሚ ነው። ይህ ስኬት አገሪቱ የገጠሟትን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፈተናዎች ተሻግራ፣ አቅሟን አስተባብራ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ለዜጎቿም ሆነ ለውጭው ዓለም የሰጠችው ትልቅ የራስ መተማመንና የተስፋ መልዕክት ነው። በአጠቃላይ፣በአንድ ጀምበር የተከናወነው ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ አርቆ የማሰብና የማቀድ ችሎታዋን ብቻ ሳይሆን፣ያቀደችውንም በአንድነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት በማውረድ በተግባር የምታሳይ ታላቅ አገር መሆኗን በግልጽ ያረጋገጠ አኩሪ ተግባር ነው።
ካቀደችው በላይ በማሳካት የአካባቢ ጥበቃ ተምሳሌትነቷን በድጋሚ ለአለም ያስመሰከረች ታላቅ ሀገር
Aug 4, 2026 114
ኢትዮጵያ በረጅም ታሪኳ ብዙ አስደናቂ ክንውኖችን አሳልፋለች፤በህዝቦቿ አይበገሬነት፣ አንድነትና ትጋት አለምን ያስገረሙ በርካታ ድሎችን ከአድዋ ድል ጀምሮ ተቀዳጅታለች። አሁን ደግሞ በ2018 ዓ.ም የክረምት ወቅት ሌላ ደማቅ ገድል ፈጽማለች። ኢትዮጵያ ትናንት በአረንጓዴ ዐሻራ 800 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር ለመትከል አቅዳ 805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኝ በመትከል ከእቅድ በላይ ማሳካቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚህም ሀገራችን ከራሷ አልፋ ለመላው አፍሪካ ታላቅ ምሳሌ መሆን መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብስረዋል፡፡ በዚህ ደማቅ ሀገራዊ የችግኝ ተከላ ንቅናቄ ላይ 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች በነቂስ ወጥተው እጅግ ከፍተኛ እና የነቃ ተሳትፎ ማድረጋቸውን በመግለጫቸው አብራርተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ላሳዩት አስደናቂ ርብርብ እና ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በዚሁ የአንድ ጀምበር ተሳትፎ 291 ነጥብ 4 ሺህ ሄክታር መሬት የአረንጓዴ ዐሻራ መልበስ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡ ይኸውም በአንድ ጀምበር 805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የራሷን ክብረ ወሰን በድጋሚ በማሻሻልና ለተቀረው አለም አዲስ ትምህርት መስጠት ችላለች። ይህ ታላቅ ሀገራዊ መርሃ ግብር አረንጓዴ ዐሻራ ከ2011 ዓ.ም አንስቶ ላለፉት ሰባት ዓመታት በስኬት ሲተገበር የቆየውና ዓለም አቀፍ እውቅናን ያተረፈው የልማት ስራ አካል ነው። በአንድ ቀን 805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን መትከል ማለት ዛፍ ከመሬት ጋር ከማዋሃድ ባለፈ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ትርጉም አለው። ይህ ድርጊት የኢትዮጵያን ህዝብ ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት፣ ዓለም አቀፋዊውን የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያደርገውን የማያቋርጥ ጥረት እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴና ምቹ የሆነች ሀገር ለማስረከብ ያለውን የላቀ ራዕይ በግልጽ ያሳየችበት ሆኗል። ይህ ግዙፍ ሀገራዊ ግብ ለማሳካት የእያንዳንዱ ዜጋ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነበር። ህፃናት፣ ወጣቶች፣አዛውንቶች፣ የመንግስትና የግል ሰራተኞች፣ ነጋዴዎች፣ አርሶ አደሮችና ሁሉም ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዚህ ታሪካዊ ቀን ከዳር እስከ ዳር በመውጣት አሻራቸውን አሳርፈዋል። ዛሬ የተከልነው እያንዳንዱ ችግኝ የነገው ተስፋችን፣የልጆቻችን ንጹህ አየር እና የሀገራችን የብልጽግና መሰረት ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር አካባቢን ከማለምለም ባለፈ፣ የዜጎችን የተቀናጀ አቅምና ሀገራዊ ራእይ ማሳያ ተደርጎ ይወሰዳል።
ኢትዮጵያ የሚለው ስም በጋራ የመቻልና የጽኑ አቋም ተምሳሌት ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Aug 3, 2026 464
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 27/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የሚለው ስም በጋራ የመቻልና የጽኑ አቋም ተምሳሌት ነው ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ፡፡ አገልግሎቱ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፏል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡- ስንትባበር ምን ማድረግ እንደምንችል ደጋግመን ለዓለም ያሳየንበት የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬም በድል ተጠናቋል። ኢትዮጵያ የሚለው ስም በጋራ የመቻልና የጽኑ አቋም ተምሳሌት ነው። መንግሥት የሀገሪቱን ዘላቂ ጥቅም ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን ሲያስቀምጥ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብም ሀገራዊ ፍላጎቱን በጋራ ተነሣሽነት እውን የማድረግ የዘመናት ልምምድ አለው። በተለይም መንግሥት ለአረንጓዴ ልማትና ሀገራዊ ከፍታ ለሚያቀርበው ጥሪ ሕዝቡ በላቀ ተሳትፎ ምላሽ የመስጠት ቁርጠኝነቱ ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ አብነት የሚሆን ነው። መንግሥት በኢትዮጵያ የተራቆቱ አካባቢዎች በልጆቿ ብርቱ እጆች እንዲታከሙ፣ እየተስፋፋ የመጣው ድርቅና በረሃማነት በዘላቂነት እንዲገታ እና በአስተማማኝ መሠረት ላይ የተገነባ አረንጓዴ ኢኮኖሚ እውን እንዲሆን ግልጽና ጽኑ አቋም በመያዝ ጥሪ ሲያቀርብ ቆይቷል። በዚህም በላቀ የሕዝብ ተሳትፎና በመንግሥት መሪነት ታላቁን የሕዳሴ ግድብ እውን ማድረግ ተችሏል፤ ኢትዮጵያዊያን ዛሬ ላይ ምድራቸውን አረንጓዴ ማልበስ ባህላቸው አድረገውታል ፤ባለፉት ሰባት ዓመታት ብቻ በአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለው ኢትዮጵያ አረንጓዴ ሸማ ለብሳለች። ዘንድሮም በንቅናቄው 8ኛው ዓመት በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን፣ በክረምቱ ደግሞ በአጠቃላይ 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል መንግሥት ቁርጠኛ አቋሙን በይፋ አሳውቋል። ለመንግሥት ሀገራዊ ጥሪ ቀናኢ የሆኑ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችም ይህንን ጥሪ በሙሉ ባለቤትነት ተቀብለው ለስኬቱ ከፍተኛ ርብርብ አድርገዋል። በዚህም በዛሬው ዕለት 26 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በአንድ ጀምበር ከ805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የተቀመጠውን ግብ ከዕቅድ በላይ አሳክተውታል። ይህ መንግሥትና ሕዘብ ሲተባበሩ ምን ማድረግ አንደሚችሉ የሚያሳይ፣ ማንም በዓለም ላይ ያለ ሀገር በቀላሉ ሊያሳካው የማይችል ድንቅ ስኬት ነው። ይህ ውጤት የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎትና የመንግሥት ስትራቴጂካዊ አቋም በአንድ አቅጣጫ ላይ እንደሚገኙ ማረጋገጫ ነው። በዛሬው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር 26 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ብርድ፣ ዝናብና ፀሐይ ሳይበግራቸው መሬት ሲያለምዱ ውለዋል፤ በዚሁ ጽኑ እንቅስቃሴም የዘንድሮው ክረምት ከገባ ጀምሮ 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተክለዋል። ኢትዮጵያ በልጆቿ ኮርታለች፤ መንግሥትም የሕዝቡን ከፍተኛ ቁርጠኝነትና ባለቤትነት ባየበት በዚህ ታሪካዊ ክስተት ከፍተኛ ኩራትና ክብር ተሰምቶታል። ይህም መንግሥት ይህንን ታላቅ ሕዝብ በበለጠ ኃላፊነትና ታማኝነት የማገልገል ጽኑ አቋሙን እንዲያጠናክር ተጨማሪ ብርታት ሆኖታል። ክቡራን ኢትዮያውያን፣ ክቡራን የኢትዮጵያ ወዳጆችና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አካላት፤ ዛሬ ይኸንን አገራዊ ራዕይ በጋራ እውን ማድረግ እንድንችል ስላደረጋችሁት ከፍተኛ ርብርብ መንግሥት በኢትዮጵያ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀርባል። የክረምቱን አጠቃላይ የ8 ቢሊዮን ችግኞች ተከላ ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የተጀመረው አገራዊ ተሳትፎና ጽኑ አቋም ተጠናክሮ ይቀጠጥላል። ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የተከልነው ችግኝ የነገ ተስፋችንን የሚያለመልም ነው- በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች
Aug 3, 2026 294
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 27/2018(ኢዜአ)፡- የተከልነው ችግኝ የነገ ተስፋችንን የሚያለመልም ነው ሲሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣቶች ተናገሩ። በሀዋሳ ከተማ 15ኛ ዙር ብሔራዊ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰልጠናን እየተከታተሉ ያሉ ወጣቶች በአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተሳትፈው አሻራቸውን አሳርፈዋል። ከበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች መካከል ወጣት መስከረም አበራ፤ሙሉጌታ ሀይሌ እና ወጣት ተመስገን አሼቦ እንዳሉት ዛሬ የተከልናቸው ችግኞች የነገ ተስፋዎቻችን በመሆናቸው ከተከላው ባሻገር የእንክብካቤው ስራ ላይ እንሳተፋለን። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እያስገኝ ካለው ጠቀሜታ ባሻገር ለቀጣዩ ትውልድ የለማች ሀገር ለማስተላለፍ ወሳኝ ምእራፍ መሆኑን ተናግረዋል። የችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ የህዝቦች አንድነትና ትስስር እያጠናከረ መምጣቱን አመልክተው ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡት የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ተሳትፎም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ ከተጀመረ ወዲህ በግብርና፣ ኢንዱስትሪና በሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ይህም ተጠናክሮ እንዲቀጥል በሚሰማሩበት አካባቢ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ለማጠናከር የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ ነው ያረጋገጡት። የስልጠውና አስተባባሪ ወይዘሮ አበባ ተገኝ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ መላው ህዝብ እየተከለ ያለው ችግኝ የቀጣዩን ትውልድ ተስፋን የሚያለመልም የጋራ ሀብት ነው ብለዋል። ባለፉት ጊዜያት በሀገሪቱ የተተከሉ ችግኞች የአፈር መሸርሸርን በማስቀረትና ለምነትን በማሳደግ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ያደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 152
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች። ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 548
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 997
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ተጠናቀቀ
Jul 29, 2026 1018
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ ከትናንት ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዘጋጅነት የተካሄደው የሁለት ቀናት ስብሰባ ላይ የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ተሳትፈዋል። ሚኒስትሮቹ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ቁልፍ አጀንዳዎችና የአፍሪካን አህጉራዊ ትስስር ማፋጠን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። በስብሰባው ሚኒስትሮቹ የአጀንዳ 2063 አፈፃፀም የሚከታተለውን ኮሚቴ ሪፖርት እንዲሁም የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እና በአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ወቅት ያሉ ስምምነቶችና የአሰራር ማዕቀፎች ያሉበትን የትግበራ ደረጃ ገምግመዋል። በተጨማሪም የ2026ቱን የህብረቱን የዓመቱ መሪ ሀሳብ የእስካአሁን የአፈጻጸም ሂደት ላይም መክረዋል። ስብሰባው እ.አ.አ. በ2017 በህብረቱ አባል ሀገራትና መንግስታት መሪዎች የፀደቀውን ተቋማዊ ማሻሻያ መነሻ ያደረገ ነው። ከስብሰባው የተገኙ ውጤቶች አህጉራዊ ዘላቂ ልማትን፣ ትስስርና ብልፅግናን እውን ለማድረግ የተቀረፀውን የአፍሪካ ህብረት የረጅም ጊዜ መሪ እቅድ (አጀንዳ 2063) ስኬታማ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ሐተታዎች
ያቀደችውን በተግባር የምታሳካ ታላቅ ሀገር
Aug 3, 2026 456
የአንድ ሀገር ታላቅነት ከሚለካባቸው ጉዳዮች አንዱ የተያዙ ሀገራዊ እቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም ዋነኛው ነው። ኢትዮጵያም በዛሬው እለት በአንድ ጀምበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አዲስ ታሪካዊ ስኬት፣ ሀገሪቱ ያቀደችውን በተግባር ማሳየት የምትችልና ትልልቅ ህልሞችን የመተርጎም አቅም ያላት ታላቅ ሀገር መሆኗን ለመላው ዓለም በተግባር ያስመሰከረ ነው። ይህ በአንድ ጀምበር የተከናወነ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በርካታ ጥልቅ ትርጉሞችን የያዘ ነው፡ በአንድ ጀንበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ግዙፍ የሎጂስቲክስ፣ የዝግጅትና የህዝብ ንቅናቄ ስራን ይጠይቃል። ይህ ስኬት ሀገሪቱ ማንኛውንም ታላቅ አገራዊ እቅድ አቅዳ እስከ መጨረሻው የትግበራ ምዕራፍ ድረስ በብቃት የመምራትና የማስተባበር ተቋማዊና ህዝባዊ አቅም እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ዕድሜ፣ ጾታ፣ ወይም ልዩነት ሳይለያያቸው በአንድ ቀን ለተመሳሳይ አገራዊ ዓላማ መቆማቸው፣ ኢትዮጵያውያን ለጋራ እድገታቸውና ለሀገራቸው የወደፊት ተስፋ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትና አንድነት አሳይቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት ዋና ስጋት በሆነበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ እርምጃ ለችግሩ መፍትሔ በመስጠት ረገድ የዓለም አቀፍ መሪነቷን ያስመሰከረችበት አጋጣሚም ጭምር ነው። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የገጠሟትን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፈተናዎች ተሻግራ፣ አቅሟን አስተባብራ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ለዜጎቿም ሆነ ለውጭው ዓለም የሰጠችው ትልቅ የራስ መተማመንና የተስፋ መልእክት ነው። በአጠቃላይ፣ በአንድ ጀምበር የተከናወነው ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ አርቆ የማሰብና የማቀድ ችሎታዋን ብቻ ሳይሆን፣ ያቀደችውንም በአንድነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት በማውረድ በተግባር የምታሳይ ታላቅ ሀገር መሆኗን በግልጽ ያረጋገጠ አኩሪ ተግባር ነው።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ ትንሳኤ ብስራት!!
Aug 2, 2026 335
በሐዊ አጫሉ መግቢያ፡- የኢንዱስትሪ ዘርፍ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬን ከሚወስኑ ዋነኛ የብልፅግና ማረጋገጫ ምሰሶዎች መካከል በግምባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ዘርፉ ምርትን ከማሳደግ ባሻገር የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የሀገር ውስጥ ምርታማነትን የሚያፋጥን የልማት ሞተር ነው። ኢትዮጵያም ከግብርና መሠረት የተነሳ ኢኮኖሚዋን ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ሁሉን አቀፍ የምርት ሥርዓት ለማሸጋገር ከምታደርገው ጥረት መካከል ኢንዱስትሪውን በቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶነት በማካተት እየሰራችበት ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ አምስት ዐበይት የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት ምሰሶዎች ተመሥርቶ እየተመራ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥ ኢንዱስትሪው የምርት አቅምን በማሳደግ የግብርና ምርቶችን ወደ ተጨማሪ እሴት በመቀየርና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ እያስገኘ ነው። ይህንን ሽግግር እውን ለማድረግ የምርት አቅምን ማሳደግ፣ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር፣ የአቅርቦት ሰንሰለትን ማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና የሰው ኃይል ልማት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ የቀድሞ ገጽታ፤ ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ለውጥ መንገድ!! በቀደሙት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለያዩ ዕድሎችንና ፈተናዎችን በማስተናገድ በርካታ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል። ሀገሪቱን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር በተደረጉ ጥረቶች የተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተገንብተዋል። እነዚህ ፓርኮችም በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የተሞከረበት ወሳኝ ምዕራፍ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ ይህ ጉዞ በበቂ መሠረተ ልማት፣ በተሟላ የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና በተቀናጀ የምርት ሰንሰለት እጥረት ምክንያት በበርካታ ፈተናዎች ለመውደቅ ተገዶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ውስንነት፣ ዕውቅትና ክህሎትን የተሰላበሰ የሰው ኃይል አለመኖር፣ የፋይናንስ እጥረት፣ ውስብስብና አስቸጋሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትና የገበያ ትስስር እጥረት የዘርፉን እድገት ገድበው የነበሩ ሁነኛ ተግዳሮቶች ናቸው። ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ምርታማነት፤ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የለውጥ ፍኖት!! ባለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ ዘርፉ የተስተዋሉ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታትና የሀገሪቱን የማምረት አቅም ለማሳደግ አዳዲስ የለውጥ አቅጣጫዎች ተነድፈው ተተግበረዋል። በተለይም ኢንዱስትሪን ከተለመደው የምርት ሥርዓት በማሻገር ወደ ተወዳዳሪ ዘመናዊና ውጤታማ የማምረቻ ማዕከል ለመቀየር የተለያዩ የፖሊሲማሻሻያዎች ተደርገዋል። የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ፣ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን፣ የሰው ኃይል አቅምን ማሳደግና የግብርና-ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር በዘርፉ የተወሰዱ ሁነኛ የለውጥ እርምጃዎች ናቸው። በዚህም የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት በማጎልበት ከሀገር ውስጥ ገበያ እስከ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ድረስ ውጤት እያስገኘ ነው። የግል ባለሃብቱ ሚና፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሞተር!! የኢንዱስትሪ ልማት በመንግሥት ጥረት ብቻ የሚሳካ አይደለም። የግል ዘርፉ በካፒታል፣ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂና በአስተዳደር ብቃት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ለዘርፉ ዕድገት የማይተካ ሚና አለው። በዚህ ረገድ የግል ባለሃብቱ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዋና አጋር እንዲሆን የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተሻሽለው እየተሰራባቸው ይገኛል። ይህም የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት በማሻሻል፣ የንግድ ሥራ ሂደቶችን በማቀላጠፍ፣ የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋትና የምርት አቅምን በማሳደግ የግሉን ዘርፉ የምርታማነት አቅም እያጎለበተ ነው። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትንሳኤ ብስራት!! በሀገራችን የኢኮኖሚ አቅጣጫ ውስጥ የምርትና አገልግሎት አሰጣጥን በማቀናጀት አዲስ ምዕራፍ ከከፈቱ ዐበይት ሀገራዊ መርሃ-ግብሮች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተጠቃሽ ነው። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማምረት ባህልን በማሳደግ ዘርፉ ወደ አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚሸጋገርበት ሁነኛ ዕድልን ፈጥሯል። ንቅናቄው የማምረት አቅምን በማሳደግ ሥራ ያቆሙ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ መመለስ፣ የአምራቾችን ችግሮች በፍጥነት መፍታትና አዳዲስ ባለሃብቶችን ወደ ዘርፉ በመሳብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤ እያበረከተም ይገኛል። በዚህ ሂደት በፋይናንስ፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በውጭ ምንዛሬና በተቋማዊ ቅንጅት ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎች የአምራች ዘርፉን የምርታማነት አቅም በማጎልበት ጉልህ ሚና ተጫውቷል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲያንሰራራ በማድረግ የምርታማነት አብዮት እንዲቀጣጠል እያደረገ ይገኛል። የንቅናቄው ዋና ዓላማ በአምራች ዘርፉ የነበሩ ማነቆዎችን በመፍታት የኢትዮጵያን የማምረት አቅም ማሳደግ ነው። ይህም ሥራ ያቆሙ ወይም በአቅማቸው ልክ ያልሠሩ ፋብሪካዎችን ወደ ሙሉ ምርት በመመለስ የአምራቾችን ችግር በተቀናጀ መንገድ መፍታት፣ የፋይናንስና የግብዓት ተደራሽነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጓል። በዚህ ሂደት የማምረቻ ዘርፉ በአዲስ የሥራ ባህል፣ በተቋማዊ ቅንጅትና በፈጣን ውሳኔ አሰጣጥ እየተመራ መሆኑ የለውጡን ፍጥነት እያሳደገው ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ተደራሽነትን ማሻሻልና የምርት ጥራትን ማረጋገጥ የኢንዱስትሪው ትንሳኤ ዋና ማሳያዎች ናቸው። ለአብነትም፡- የፋይናንስ አቅምና የብድር አቅርቦት ማሻሻል፡- የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ እንቅፋት የሆነውን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ በተደረገው ርብርብ፣ የብድር አቅም ቀደም ሲል ከነበረበት 40 ቢሊዮን ብር ወደ 115 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ለአምራቾች ሰፊ የካፒታል አቅም መፍጠር ተችሏል። የውጭ ምንዛሬ ግኝትና የግብዓት ድጋፍ ማደግ፡- ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ይቀርብ የነበረው የውጭ ምንዛሬ መጠን አሁን ላይ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንዲደርስ ተደርጓል። ይህም ፋብሪካዎች ከአቅማቸው በታች እንዲሠሩ ያስገድድ የነበረውን የምርት ውስንነት በከፍተኛ ደረጃ አቃሎታል። የምርት ዕድገት፣ ተኪ ምርትና የኤክስፖርት አፈጻጸም፡- ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ ከነበረበት 348 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5.9 ቢሊዮን ዶላር በማደግ ግዙፍ ሀገራዊ ድል ተመዝግቧል። እንዲሁም በኤክስፖርት ገበያ የሚገኘው ገቢ ከ385 ሚሊዮን ዶላር ወደ 607 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ማለት ችሏል። ተቋማዊ ቅንጅትና አዲስ የሥራ ባህል ማዳበር፡- በክልሎችና በፌዴራል ተቋማት መካከል የነበረውን የቢሮክራሲ ጫና በመቀነስ ፈጣን ውሳኔዎች እንዲሰጡ መደረጉ፤ እንዲሁም ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርትን በኩራት የመጠቀም እና የሀገር ፍቅር ስሜትን ከአምራችነት ጋር የማስተሳሰር ትልቅ ማህበራዊ ንቃተ-ህሊና መገንባት ተችሏል። የወደፊት ተስፋ፤ ኢትዮጵያ አዲሲቷ አፍሪካዊት የኢንዱስትሪ ምርታማነት ተምሳሌት ሀገር!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ በቀጣይ ዓመታት ከተለመደው ማምረት ወደ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ሥርዓት እንዲሸጋገር ይጠበቃል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሜሽን፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና የፈጠራ ሥርዓቶችን ወደ ማምረቻ ዘርፉ ማስገባት የወደፊቱ ትኩረት ይሆናል። በተመሳሳይም ጠንካራ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስር፣ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት፣ ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአህጉራዊ ገበያ ተደራሽነት የሀገሪቱ ቀጣይ የኢንዱስትሪ ግቦች ናቸው። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) የሚፈጥረውን ሰፊ የገበያ ዕድል በመጠቀም ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችል መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ማጠቃለያ፡- ማምረት፤ የኢትዮጵያ የብልፅግና ቁልፍ መሳሪያ!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ተጨማሪ እሴት ያለው ምርት አቅራቢነት በማምራት እመርታዊ ውጤቶችን እያስገኘ ነው። የኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ማለት ፋብሪካዎችን ብቻ ማስፋፋት ሳይሆን የሀገርን ምርታማነት፣ የወጣቶችን ዕድል፣ የኢኮኖሚ ነፃነትንና የልማት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን የዛሬ ልማት ብቻ ሳይሆን የነገውን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚገነባ ሀገራዊ ራዕይ ነው።
የክልሎች ቅኝት - በወፍ በረር
Aug 2, 2026 221
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 26/2018 (ኢዜአ) የክልሎች ቅኝት - በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግብርናውን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ድርሻ አበርክተዋል። በክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5 ዓመት 3ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የተጠናቀቀውን በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም በክልሉ የግብርናውን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱን አንስተዋል። የሜካናይዜሽን እርሻም ተግባራዊ በመደረጉ ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱንም ጠቅሰዋል። ከማዕድን ዘርፍም በበጀት ዓመቱ ከ 8 ሺህ 900 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል። ኦሮሚያ ክልል በኦሮሚያ ክልል የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ግልጽ እና ተጠያቂነት ያለበት በማድረግ የሙስና እና የብልሹ አሰራር ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ሪፎርም እየተተገበረ ይገኛል። ለዚህም የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራ ይፋ የማድረጊያ መርሃ ግብር ''የአገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ለሁለንተናዊ ብልጽግና'' በሚል መሪ ሀሳብ በቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል። የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ የመንግስትን አገልግሎት አሰጣጥን የተሳለጠ ለማድረግ የሚያስችል እስከ ቀበሌ የደረሰ አሰራር መዘርጋቱን በወቅቱ አንስተዋል። አልግሎቶችን በዲጂታል ስርዓት በመደገፍ የህዝቡን እንግልት፣ ጊዜና ወጪ በመቆጠብ ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል። ይህም በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ሲዳማ ክልል የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ የ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት ንቅናቄ መድረክ ላይ በመገኘት ባደረጉት ንግግር በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ሥራ ምቹ ማድረግና በግብአት ለማሟላት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ስራ ምቹ በማድረግ በትምህርት ጥራት ላይ አዎንታዊ ለውጥ እንዲታይ መደረጉንም አስረድተዋል። ጋምቤላ ክልል የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ''ተስፋን እንትከል'' በሚል መሪ ሀሳብ የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማጃንግ ዞን በመንገሺ ወረዳ ያስጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። በክልሉ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን ለማረጋገጥ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራዎች በህዝብ ተሳትፎ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል ። ባለፉት ዓመታት የተከናወኑት የአረንጓዴ አሻራ ልማት የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ ከማድረጋቸው ባለፈ የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻሉንም ርዕሰ መስተዳድሯ ገልፀዋል። አማራ ክልል በአማራ ክልል የግብርናን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለኢንዱስትሪዎች ግብአት ማምረት ተችሏል። የዚሁ አካል የሆነው በክልሉ በሰሜን ሸዋ ዞን በሞረትና ጅሩ ወረዳ 837 አርሶ አደሮች በማህበር በመደረጃት “የጅሩ-አግሮ ቢዝነስ“ ኩባንያን መስርተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት ኩባንያው የአርሶ አደሮችን ምርት በማቀነባበር ለገበያ የሚያቀርብ ነው። የአግሮ-ቢዝነስ ኩባንያውም ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አርሶ አደሩ ከጥሬ ግብአት አቅራቢነት ወደ አምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስተርነት በማደግ ላይ መሆኑን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል። ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳዳር ዙሪያ ጨታ ቀበሌ የተገነባውን የባቾ ገጠር ሞዴል መንደር መርቀው ለነዋሪዎች አስረክበዋል። በወቅቱም የሞዴል የገጠር መንደሩ መገንባት የሌማት ትሩፋት ስራዎችን ውጤታማ በማድረግ የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ አቅም ለማሳደግ ብሎም ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። በሌላ በኩል በክልሉ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ገንብቶ በማጠናቀቅ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በተለይም የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በመገንባት የወረዳና ቀበሌዎች ማህበራዊ ትስስር እንዲጠናከርና የግብይት ሰንሰለትም እንዲቀላጠፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። ለአብነትም በክልሉ ኮንታ ዞን በአመያ ዙሪያ ወረዳ በኡማ ወንዝ ላይ የተገነባው ድልድይ የአካባቢውን ነዋሪዎች የዘመናት ችግር ያቃለለና ለመሰረተ ልማት ጥያቄያቸው ምላሽ የሰጠ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ በክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ማስተዋወቂያ መድረክ ላይ በመገኘት ንግግር አድርገዋል። በመልእክታቸውም በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት እየተደረገ ባለው ጥረት ውጤት እየተገኘ ስለመሆኑ ተናግረዋል። በ2019 በጀት ዓመትም በክልሉ በተደራጀ ህዝባዊ ንቅናቄ 48 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ግብር ለመሰብሰብ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል። ለዚህም በህግና የአሠራር ስርአት በመታገዝ የገቢ አቅምን በማስፋት የክልሉን ዕድገት ዘላቂነት በማረጋገጥ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቀዋል። በተመሳሳይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር ጉባኤ በአርባ ምንጭ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት እየተደረገ ባለው ጥረት ውጤት እየተገኘ ነው ብለዋል ። በ2019 በጀት አመትም የክልሉን የገቢ አቅም ለይቶ በተደራጀ ህዝባዊ ንቅናቄ የግብር እቅድን ለማሳካት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በዚህም በበጀት አመቱ 48 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል። ገቢውን ለማሳካትም የህግና የአሠራር ስርአት በመዘርጋት የክልሉ ዕድገት በዘላቂነት በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቀዋል። አፋር ክልል በአፋር ክልል የእንሰሳትና ዓሳ ሀብትን በማልማት ለወጣቶች የስራ እድልን ለማስፋት የተሰሩ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የክልሉ የእንሰሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ ኀላፊ አቶ ኢብራሂም መሐመድ ገልጸዋል። ለዚህም ስምንት የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሐይቆች ላይ ወጣቶችን አደራጅቶ ወደ አሳ ልማት ስራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል። ለአብነትም በአፋምቦ ሐይቅ ላይ 200 ወጣቶች በዓሳ ሀብት ልማት ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ የሚሆኑበት አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል። በዓሳ ሀብት ልማቱ ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች እንዳሉት የአሳ ሀብትን አልምተው ተጠቃሚ ለመሆን በማህበር ተደራጅተው በመስራት ላይ ናቸው። ስራውንም ለማሳካት ክልሉ እያደረገ ያለው የሙያ ስልጠናና ድጋፍ የማይተካ ድርሻ አለው ብለዋል። ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል "ሁሉ አቀፍ እመርታ ፣ ለሁለንተናዊ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራ አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የከፍተኛ አመራሮች የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል። ርዕስ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል። የህዝቦችን አብሮነት በማጠናከር ክልሉን የህብረ ብሄራዊነት ተምሳሌት ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል። በበጀት ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችን ማጠናከርና የተስተዋሉ ጉድለቶችን በማረም ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ የመድረኩ ዋና ዓላማ ስለመሆኑም ገልጸዋል። ሐረሪ ክልል የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሃላፊ ሮዛ ኡመር እንደገለፀት፤ በክልሉ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ስራ በገጠር ወረዳዎች የመስኖ ልማት በስፋት ተከናውነዋል። ተግባሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ የ2018 የግብርና ልማት እቅድ አፈጻጸምና የ2019 የግብርና ልማት መሪ እቅድ ላይ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የእንስሳት ተዋጽኦና የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ትልቅ እመርታ የተገኘበት ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባሻገር የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ ተወጥቷል ብለዋል። ሶማሌ ክልል የሶማሌ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባዔውን ሲያካሂድ ርእሰ መስተዳድሩ ሙስጠፌ ሙሀመድ፤ የተጠናቀቀውን በጀት ዓመት ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም በክልሉ የሰላምና የልማት እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ስራዎችና የመጡ ውጤቶችን አብራርተዋል። የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው፤ የፍትህ አካላትን አቅም ለመገንባት በተደረገ ጥረት የፍትህ ሂደቱ የተሳለጠ እንዲሆን መቻሉንም አንስተዋል። በክልሉ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በድህነት ቅንሳ፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እንዲሁም በተፈጥሮና በሰው ሠራሽ የሚመጡ አደጋዎች ቅነሳም ከፍተኛ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
ከሀገር አቀፍ ንቅናቄ እስከ ዓለም አቀፍ እውቅና፦የአረንጓዴ አሻራ ውጤታማ አበርክቶ
Jul 30, 2026 550
በታዋቂ ዓለም አቀፍ የሳይንስ መጽሔቶች ላይ የታተሙ ተከታታይ ጥናቶች የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር በደን መልሶ ማልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተዕፅኖን በመከላከል ፣ የካርበን ክምችት በማሳደግ እና በማህበረሰብ ተሳትፎ ረገድ ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ መሆኑን አረጋገጡ። የጥናቱ ግኝቶች ከስምንት ዓመታት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)አነሳሽነት የተጀመረው የአረጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር፣ በአፍሪካ ግዙፍ እና እጅግ ውጤታማ ወደሆነ የመሬት ገጽታ መልሶ ማልማት ፕሮግራም ማደጉን የሚያሳይ ጠንካራ ሳይንሳዊ ማስረጃ አቅርበዋል። ኔቸር ፖርትፎሊዮ (Nature Portfolio)፣ ኤልሴቪየር (Elsevier) እና ስፕሪንገር (Springer)ን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባላቸው አሳታሚዎች እ.ኤ.አ. በ2026 የወጡ አምስት ጥናቶች፤ የሳተላይት ምስሎችን፣ የመስክ የዳሰሳ ጥናቶችን፣ የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂዎችን እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም የመርሐ-ግብሩን አካባቢያዊ ፋይዳ ገምግመዋል። ከፍተኛ የችግኝ ጽድቀት ምጣኔ - የውጤታማ መልሶ ማልማት ማሳያ በኤልሴቪየር 'ትሪስ፣ ፎረስስ ኤንድ ፒፕል' (Trees, Forests and People) መጽሔት ላይ የታተመ ጥናት (አሰፋ እና ሌሎች፣ 2026) እንዳመለከተው፣ በደቡብ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የተተከሉ የዛፍ ችግኞች 80 በመቶ የሚገመት የጽድቀት ምጣኔ አስመዝግበዋል፤ ይህም ከሌሎች በርካታ ሰፊ የደን ልማት ፕሮግራሞች ልቆ የተገኘ ነው። ተመራማሪዎቹ ለዚህ ስኬት በዋነኛነት የጠቀሷቸው የተሻሻሉ የመልሶ ማልማት ልምዶችን ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል በዋናው የክረምት ወቅት መትከል፣ ጥንቃቄ የተሞላበት የቦታ ምርጫ፣ እንዲሁም በቴክኒክ ስልጠና የታገዘ ጠንካራ ማህበረሰብ አቀፍ እንክብካቤ ይገኙበታል። የጥናቱ መሪ ዶ/ር ታደሰ አሰፋ እንደገለጹት፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ከሳይንሳዊ የደን አያያዝ ጋር ማቀናጀት አዳዲስ ተከላ የተካሄደባቸው አካባቢዎች ጊዜያዊ የችግኝ መትከያ ቦታዎች ብቻ ሆነው ከመቅረት ይልቅ ዘላቂ ወደሆነ ደንነት እንዲያድጉ አስችሏል። የማህበረሰብ ተሳትፎ ለስኬቱ ሞተር ነው በስፕሪንገር 'ዲስከቨር ኢንቫይሮመንት' (Discover Environment) ላይ የታተመ ሌላ ጥናት ደግሞ ሰፊው የማህበረሰብ ተሳትፎ የመርሐ-ግብሩ ታላቅ ጥንካሬ መሆኑን አመልክቷል። የጥናቱ መሪ ዶ/ር አብዱረዛቅ ሀጂ እንዳስገነዘቡት፣ እያደገ የመጣው የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ እና በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ የህዝብ ተነሳሽነት፣ አባወራዎች ችግኝ መትከልን የአካባቢን የመቋቋም አቅም ለመገንባት፣ ለዘላቂ ግብርና እና ለወደፊት የኑሮ መሰረት እንደተደረገ ኢንቨስትመንት እንዲመለከቱት አድርጓል። የህዝብ ተሳትፎ የመርሐ-ግብሩ የረጅም ጊዜ ስኬት የማዕዘን ድንጋይ መሆኑን ጥናቱ በማጠቃለያው አስቀምጧል። የደን ሽፋን ማደግ የአካባቢን አየር ንብረት ያሻሽላል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ቡኖ በደሌ ዞን የተካሄደ ጥናት በስድስት ዓመታት ውስጥ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን፣ ማለትምከ27.64 በመቶ ወደ 38.24 በመቶ ከፍ ማለቱን አስመዝግቧል። ጥናቱ የመሬት ገጽ የሙቀት መጠን እስከ 1.16 ዲግሪ ሴልሺየስ መቀነሱን ያረጋገጠ ሲሆን፣ ይህም የደን ሽፋን መስፋፋትየአካባቢውን አየር ንብረት እያሻሻለ እና የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅምን እያጠናከረ መሆኑንያሳያል። እነዚህ ለውጦች የስነ-ምህዳር አገልግሎቶችን እንደሚያሳድጉ እና የግብርና ምርታማነትን እንደሚደግፉ ይጠበቃል ሲሉ ተመራማሪዎቹተናግረዋል። ጥናቶች ከፍተኛ የካርበን ክምችት አቅም መኖሩን አጉልተዋልበኔቸር ፖርትፎሊዮ (Nature Portfolio) ሥር በ'ሳይንቲፊክ ሪፖርትስ' መጽሔት ላይየወጣ ሌላ ጥናት፣ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የዛፍ ዝርያዎች እና የግብርና-ደን ሥርዓቶች ከፍተኛ መጠንያለው የካርበን ዳይኦክሳይድ ክምችት የመያዝ አቅም እንዳላቸው አረጋግጧል። አንዳንድ መልመው ያገገሙ መሬቶች በሄክታር ወደ 500 ሜጋግራም የሚጠጋ የካርበን ዳይኦክሳይድ መጠን የያዙ መሆናቸው የተረጋገጠሲሆን፣ ይህም መርሐ-ግብሩ የአየር ንብረት ለውጥን በማቃለል ረገድ ያለውን ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያሳያል። የደን መልሶ ማልማት ስራውን ማስፋፋት የኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት እርምጃ ተሳትፎ የበለጠ እንደሚያጠናክርናበማደግ ላይ ባለው የዓለም አቀፍ የካርበን ገበያ ላይ ዕድሎችን እንደሚፈጥር ተመራማሪዎቹ ገልጸዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የደን ዕድገቱ እንደሚቀጥል ተንብዮአል ማሽን ለርኒንግ፣ የሳተላይት ምስሎች እና የጂኦስፓሻል ትንታኔዎችን በመጠቀም በስፕሪንገር 'ኢንቫይሮመንታል ሞኒተሪንግ ኤንድአሴስመንት' (Environmental Monitoring and Assessment) መጽሔት ላይ የታተመ ሌላ ጥናት እንዳመላከተው፣አሁን ያለው የመልሶ ማልማት ጥረት ከተቀጠለ የኢትዮጵያ የደን ሽፋን ቢያንስ እስከ 2035 ድረስ መስፋፋቱን እንደሚቀጥልተንብዮአል። በመሬት ገጽታ መልሶ ማልማት ላይ የሚደረገው ተከታታይ ኢንቨስትመንት የደን ሽፋንን የበለጠ እንደሚያሳድግ፣ የካርበን ክምችትንእንደሚያጠናክር እንዲሁም የኢትዮጵያን የአየር ንብረት እና የዘላቂ ልማት ግቦችን እንደሚደግፍ ጥናቱ ያሳያል። ዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ እውቅና በአጠቃላይ ሲታይ፣ አምስቱ ገለልተኛ ጥናቶች የኢትዮጵያን አረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ሁለንተናዊ ሳይንሳዊ ግምገማ በማቅረብ፤በደን መልሶ ማልማት፣ በካርበን ክምችት፣ በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም እና በህዝብ ተሳትፎ ረገድ የሚለኩና ተጨባጭ ውጤቶችንማምጣቱን ደምድመዋል። እነዚህ ግኝቶች የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የሰፊ ሥነ-ምህዳር መልሶ ማልማት ቀዳሚ ሞዴል በማድረግ ያስቀመጡትሲሆን፤ ዘላቂ የፖለቲካ ቁርጠኝነት፣ ሳይንሳዊ ዕቅድ እና አገር አቀፍ የህዝብ ንቅናቄ እንዴት ተጨባጭ የአካባቢ ጥበቃ ውጤቶችንማምጣት እንደሚችሉና፣ ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ እና የመሬት መራቆትን ለመከላከል ለሚደረጉ ጥረቶች ከፍተኛ አስተዋጽዖእንደሚያበረክቱ በጉልህ አሳይተዋል።
ትንታኔዎች
በተቃርኖ የተሞላው ሕገ ወጡ ሕወሓት የጥፋት ጉዞ
Jul 30, 2026 507
የሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የፖለቲካ ጉዞ በበርካታ መሠረታዊ ተቃርኖዎችና የፖለቲካ ስህተቶች የተሞላ ነው። ቡድኑ በትግል ጊዜም ይሁን ሀገርን በመምራት ባደረገው የፖለቲካ ተሳትፎ ታሪክ ይቅር የማይላቸው ስህተቶችን ፈጽሟል። ከሁሉም በላይ የትግራይን ሕዝብ ለዘመን ተሻጋሪ መከራና ስቃይ ዳርጓል። የወጣቶችን ተስፋ እና ሕልም አጨልሟል። የሕገ ወጡ ቡድን በተቃርኖ የተሞላ ጉዞ በጨረፍታ እንመልከት። ተቃርኖ አንድ፦ የሀገር ገዥነት እና የነጻ አውጪነት መንፈስ ሕገ ወጡ ሕወሓት ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ግንባር ፈጥሮ ሀገር በመራበት ዘመንም ጉዞው በተቃርኖ የተሞላ ነበር። በዚህ የሥልጣን ዘመኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ከአንድነት ይልቅ ልዩነትን፤ ከኅብረት ይልቅ መነጠልን ሥር እንዲሰድ አድርጓል። በስም ደረጃ ሕብረ ብሔራዊ የፌዴራል ሥርዓት እንደሚያራምድ ቢናገርም ለኢትዮጵያውያን የተለያየ የዳቦ ስም በመስጠት እርስ በእርስ እንዲጠራጠሩ በማድረግ የጥላቻ ፖለቲካን አንግሷል። የሕግ የበላይነት እና የሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት በአንዱ ቡድን ላይ የማይተገበር ሌላው ላይ ግን ተግባራዊ እንዲሆን አድርጓል። ከቡድኑ ጋር የጥቅም ትስስር ያላቸው ቡድኖች ለሕግ የማይገዙ፣ ከኮንትሮባንድ እስከ ዓለም አቀፍ ወንጀሎች ውስጥ የሚሳተፉ ነበሩ። ሌላው ጽንፈኛ፣ አክራሪ እና ተስፋፊ ተደርጎ በሽብር እየተወነጀለ በየማረሚያ ቤቱ እንዲንገላታ ተደርጓል። በጥቅሉ ሕገ-መንግሥት እና የፌዴራል ሥርዓትን ለራሱ በሚያመች መልኩ ሲጠቀምበት ቆይቷል። ከዚህም ባለፈ ሕገ ወጡ ቡድን ሀገርን እየመራ እንደ አንድ የክልል ነጻ አውጪ ድርጅት በብሔሮች መካከል ጥርጣሬና ልዩነት እንዲሰፋ የሚያደርጉ የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካዎችንም አንግሷል። ‘እኛ እና እነሱ’ የሚል ፖለቲካን ከማካሄድ ባለፈ ‘ልዩ ኃይል’ በሚል ወታደራዊ አደረጃጀት ፈጥሮ መንግሥት መስሎ ሀገርን የማፍረስ እና የማዳከም ተግባር ውስጥ ተሳትፏል። ተቃርኖ ሁለት፦ ሰሜን እዝን ባጠቃበት ጊዜ ሕገ ወጡ ቡድን ራሱ ያደራጀውን እና ሲያሞካሸው የቆየውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 2013 ዓ.ም. በማጥቃት የተቃርኖ ጉዞውን መቀጠሉን አረጋግጧል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን እዝ የትግራይ ሕዝብ ጋሻና መከታ፣ የችግር ጊዜ ደራሽ እና ከሻዕቢያ ተከላካይ ሆኖ ላቡንና ደሙን ገብሯል። ሕገ ወጡ ቡድን የሀገር ሉዓላዊነትና የሕገ-መንግሥት ጠባቂ ነኝ ሲል ቆይቶ፣ ለ20 ዓመታት በትግራይ ሕዝብ ደህንነት ጥበቃ ላይ የነበረውን እና የትግራይ ተወላጆችንም በሠራዊቱ ውስጥ ያቀፈውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት አጥቅቷል። ሴረኛው እና በተቃርኖ የተሞላው ቡድን የማይመርዝና የማይለውጠው መሆኑን ያረጋገጠበትን ድርጊት ፈጽሞ የሀገር ጋሻና መከታን አዋርዷል። ይህ ድርጊት በኢትዮጵያ ዘመናዊ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እጅግ አሳፋሪ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል። የተቃርኖው ውጤት ግን መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ባልተጠበቀ ሁኔታ አንድ ላይ አስተሳሰረ፤ ለሉዓላዊነትና ለግዛት አንድነት የአባቶቹን ታሪክ እንዲደግም ዕድል ፈጠረ። ተቃርኖ ሦስት፦ የሰላም ውል እና የውስጥ ክፍፍል ሕገ ወጡ ቡድን የሥልጣን ጥመኝነቱን ለማርካት ስፍር ቁጥር የሌላቸው የትግራይ ክልል ተስፋ የሆኑ ወጣቶችን በጦርነት ከማገደ በኋላ የሰላም ስምምነት ተፈረመ። በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ጦርነቱን ለማስቆም የተደረገ ወሳኝ እርምጃ ነበረ። ነገር ግን ከስምምነቱ በኋላ አሁንም ከስህተቱ የማይማረው ይህ ቡድን የተቃርኖ ጉዞውን መቀጠሉን ያረጋገጠበት ጥፋት ፈጸመ። ሕገ ወጡ ቡድን ስምምነቱን በይፋ ከተቀበለው በኋላ ስምምነቱን የሚጥሱ ድርጊቶችን መፈጸም ቀጠለ። መሣሪያ ለማስረከብ ተስማምቶ በስምምነቱ መሠረት መሄድ አቃተው፣ እንቅፋት ፈጠረ። በትጥቅ ውስጥ የቆዩ ወጣቶች ወደ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመለሱ ማድረግ ነበረበት፣ አላደረገም። ይልቅስ ለሌላ ጥፋት ውስጥ ለውስጥ መዘጋጀቱን ተያያዘው። ጊዜያዊ አስተዳደር ለመመስረት ተስማምቶ ወደ ተግባር ከተገባ በኋላ የጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮችን አልቀበልም በማለት ሕገ ወጥነቱን ቀጥሎ ለትግራይ ሕዝብ ሰላም እና እፎይታ የሰጠውን የሰላም ስምምነት አፈረሰ። ከጦርነቱ ማብቃት በኋላ ትኩረት መደረግ የነበረበት የወደሙ አካባቢዎችን መገንባት፣ የተፈናቀሉትን መመለስ እና ሰብዓዊ እርዳታ ማፋጠን ላይ መሆን ሲገባው፣ ሕገ ወጡ ቡድን ወደ ውጭ ይፋ በወጣ የሥልጣን ሽኩቻና የእርስ በእርስ ውንጀላ ውስጥ መዘፈቁ ለሕዝቡ ያለው ግድየለሽነት ማሳያ ሆኖ ተወሰደ። ለጥፋት ተልዕኮው ስኬት በፍጹም የዓላማም ይሁን የትግል አንድነት የለኝም ሲላቸው ከነበሩ የጥፋት ቡድኖች ጋር አበረ። ይህ ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመመሳጠር ሉዓላዊነትን ለማስደፈር እና ሀገር ለማፍረስ በሙሉ አቅሙ መንቀሳቀስ ጀመረ። ልብ ማለት የሚገባን ባህር በርን የሚያክል ጉዳይ እንደ ተራ ሸቀጥ ያየው ቡድን እንዴት ስለ ብሔራዊ ክብር እና ሉዓላዊነት ሊያስብ ይችላል? ሊሆን አይችልም። ተቃርኖ አራት፦ የሕገ ወጡ ቡድን የመጨረሻው የጥፋት ጉዞ ዓለምና የኢትዮጵያ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ሁኔታ በከፍተኛ ሁኔታ ቢቀየርም፣ ሕገ ወጡ ሕወሓት ግን አሁንም በ1960ዎቹ እና 70ዎቹ የትግል ስልት ተከተሏል። ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከሆኑት ባዕዳን ተልዕኮ ተቀብሎ ከሀገር ውስጥ ባንዳዎች ጋር አብሯል። ‘ጽምዶ’ ከተባለው የጥፋት ስብስብ ፊት አውራሪ በመሆን የለመደውን የተቃርኖ ጉዞ ለመቀጠል ተቅበዝብዟል። የወጣቱን የሥራ፣ የዲሞክራሲ፣ የኢኮኖሚና የዘመናዊነት ጥያቄ በትክክለኛ መንገድ ከመመለስ ይልቅ ወደ ሥልጣን ለመመለስ ለሚያደርገው የቀቢጸ ተስፋ ሙከራ እያደረገ ነው። ከምርጫ ቦርድ ጋር ያለው ሕጋዊ ሰውነት የማጣት አለመግባባት እና በሕጋዊ መንገድ ራሱን ለማደስ ፈቃደኛ አለመሆኑ ቡድኑን በሕግ ፊትም ሆነ በፖለቲካዊ ምህዳሩ ውስጥ ወደ መጨረሻው የመገለልና የውድቀት ምዕራፍ መርቶታል። ዛሬ ግን ትናንት አይደለም። ኢትዮጵያ ዘመኑን በዋጀ አመራር እየተመራች ትገኛለች። ዘመኑን ሙሉ የተቃርኖ ጉዞ ያደረገው ሕገ ወጡ ቡድን ወደ መጨረሻው የፖለቲካ ውድቀት እያመራ ነው። የሕገ ወጡ ቡድን የተቃርኖ ጉዞም የበቃል።
የኢትዮጵያዊያን ምክክር፤ የጋራ ነገን የሚያሻግር የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ድልድይ
Jul 22, 2026 868
በሚኪያስ ጎቡ መግቢያ፡- ሀገራት ከጦርነት በላይ የሚፈትናቸው ጠላት አለ፤ እርሱም በአንድ ሀገር ልጆች መካከል የሚፈጠረው የመተማመን መሰናክል ነው። መሣሪያ የፈጠረውን ጉዳት እንደገና መገንባት ይቻላል። የተሰበረ ልብና የጠፋ መተማመን ግን በጉልበት አይመለስም። ለዚህም ነው ብዙ ሀገራት ከግጭት በኋላ ወደ ምክክር የሚመለሱት። ብሔራዊ ምክክር የአንድ መንግሥት ፕሮጀክት ወይም የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአንድ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፈው የሰላም ውርስ ነው። የሚጋጩ ሃሳቦች በጠመንጃ ሳይሆን በቃል ሲገናኙ፣ የተለያዩ ትርክቶች በመደማመጥ ሲቀራረቡ፣ ልዩነቶችም የጥላቻ ምንጭ ሳይሆኑ የመግባባት መነሻ ሲሆኑ ነው እውነተኛ ሀገራዊ ምክክር የሚፈጸመው። የዓለም ተሞክሮ እንደሚያሳየው ብሔራዊ ምክክር አንድ ዓይነት ቀመር የለውም። እያንዳንዱ ሀገር በታሪኩ፣ በባህሉ፣ በፖለቲካዊ እውነታውና በማኅበራዊ መዋቅሩ መሰረት የራሱን መንገድ ይመርጣል። ነገር ግን የሁሉም ግብ አንድ ነው፤ ግጭትን በመግባባት፣ ጥላቻን በመተማመን፣ ፍርሃትን በተስፋ መተካት። በአውሮፓ ከኮሙኒዝም ውድቀት በኋላ፣ በአፍሪካ ከአምባገነናዊ አስተዳደሮች ሽግግር ወቅት፣ በደቡብ አሜሪካ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሂደቶችና በዓረቡ ዓለም ከፖለቲካ አብዮቶች በኋላ የተካሄዱ ምክክሮች አንድ ትልቅ ትምህርት ይሰጣሉ። ምክክር ሲታመን ሀገር ያድናል፤ ለፖለቲካ ጥቅም ሲውል ግን ቀውስን ያባብሳል። ይህ የኢትዮጵያም ትልቁ ፈተና ነው። ሀገራዊ ምክክር የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት ነው። የምንናገረው ቃል፣ የምንጽፈው ሐሳብ፣ የምናዳምጠው አቋምና የምንቀበለው ልዩነት የነገዋን ኢትዮጵያ ይቀርጻሉ። ምክክር የሚጀምረው በአዳራሽ ሳይሆን በሰዎች ልብ ውስጥ ነው፤ የሚሳካውም ከመናገር በላይ በመደማመጥ ሲቻል ነው። ስለዚህ የዛሬው ጥያቄ "ምክክር ይካሄድ ወይ?" የሚል አይደለም። "ምክክሩን ለሀገር የሚበጅ፣ ለትውልድ የሚተርፍ፣ ለታሪክ የሚያስከብር እንዴት እናድርገው?" የሚለው ነው። መልሱም በአካታችነት፣ በእውነት፣ በመከባበርና በሀገርን ከግል ጥቅም በላይ በማስቀደም ውስጥ ይገኛል። ምክክር፤ የሀገር መድኃኒት ወይስ የትውልድ ፈተና? ምክክር ለምን ያስፈልጋል?፡- ማንኛውም ሀገር የሚያድገው በሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ግንባታ ብቻ አይደለም። በሕዝቦቿ መካከል በሚኖረው መተማመን ጭምር እንጂ። መንገድ፣ ድልድይና ፋብሪካ መገንባት ይቻላል፤ ነገር ግን የተሰበረ ማኅበራዊ ትስስር ካልተጠገነ የልማቱ መሠረት ይናወጣል። ስለዚህ ብሔራዊ ምክክር የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን የሀገር የወደፊት ዕጣ ፋንታ የሚወሰንበት የጋራ አስተሳሰብ ሂደት ነው። የምክክሩ ዋና ዓላማ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር አይደለም። ይልቁንም ሁሉም ወገኖች የራሳቸውን እውነት እየገለጹ፣ የሌላውንም እውነት በማዳመጥ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ሂደት ነው። እውነተኛ የምክክር ድል የሚለካውም የማን ሃሳብ አሸነፈ ሳይሆን ለሀገር ምን ያህል ሰላምና መተማመን ፈጠረ በሚለው ነው። የዓለም ተሞክሮ የሚያስተምረን፡- የታሪክ ገጾች እንደሚያሳዩት ሀገራት የብሔራዊ ምክክርን መንገድ የመረጡት ሌሎች አማራጮች ሲያቅቷቸው ነው። አንዳንዶቹ የረዥም ጊዜ የፖለቲካ ቀውስ ነበራቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በሥልጣን ሽኩቻ ተከፋፍለው ሲራኮቶ የሰነባበቱ ናቸው። ነገር ግን የተሳካላቸው ሀገራት አንድ የጋራ መርህ ነበራቸው፤ የሀገርን ጥቅም ከፓርቲ፣ ከቡድንና ከግል ጥቅም በላይ አስቀድመዋል። ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ወደ ዴሞክራሲ የተሸጋገረችው በበቀል ሳይሆን በሰለጠነ ምክክር ነው። ፖላንድና ሀንጋሪ የፖለቲካ ሽግግራቸውን በየጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር አሳልፈዋል። ላይቤሪያና ሊባኖስ የጦርነት ቁስላቸውን ለማዳን የመደማመጥን መንገድ መርጠዋል። በተቃራኒው ግን ምክክርን ለፖለቲካ ሕጋዊነት ማግኛ፣ ለሥልጣን ማራዘሚያ ወይም ለውጭ ጫና ማስታገሻ ብቻ ያደረጉ ሀገራት የበለጠ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። ይህም አንድ ግልጽ ትምህርት ይሰጠናል፤ የምክክር ስኬት የሚወሰነው በመድረኩ ሳይሆን በተመካካሪዎች ቅንነት መሆኑን ያስረዳናል። ምክክር የሚጠይቀው ከባድ ኃላፊነት፡- ሀገራዊ ምክክር የኮሚሽን ወይም የመንግሥት ሥራ ብቻ አይደለም። የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነትን የሚጠይቅ የጋራ ነገ አሻጋሪ ድልድይና የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ነው። ፖለቲከኛው የሀገርን ጥቅም ማስቀደም፣ የሚዲያው እውነትን በሚዛናዊነት ማቅረብ፣ የሲቪክ ማኅበራት የተገለሉ ድምፆችን ማሰማት፣ የኃይማኖት ተቋማት ይቅርታና መቻቻልን ማስፋፋት፣ ወጣቱ ከጥላቻ ይልቅ ውይይትን መምረጥና ምሁራን በማስረጃ የተደገፈ ሃሳብ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ማንም ወገን የራሱን አቋም ብቻ ለማስገደድ ከሞከረ፣ ምክክሩ ወደ ክርክር ይቀየራል። ሁሉም ለመረዳት እንጂ ለማሸነፍ ካልመጡ ደግሞ የምክክሩ መንፈስ ይጠፋል። የሀገራዊ ምክክር ትልቁ ድል የሌላውን አቋም መለወጥ ሳይሆን፣ የሌላውን ህመም መረዳት ነው። ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር፤ ልዩነታቸው ምንድን ነው?፡- ብዙ ጊዜ ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር የሚሉት ቃላት በአንድ ትርጉም ይጠቀሳሉ። ነገር ግን በፖለቲካዊና በማኅበራዊ ሂደቶች እያንዳንዳቸው የተለየ ዓላማና ባህሪ አላቸው። ይህንን ልዩነት አለማወቅ ሀገራዊ ምክክርን ከመጀመሪያው ሊያዛባው ይችላል። ውይይት የሐሳብ ልውውጥ ነው። ሰዎች ስለ አንድ ጉዳይ አመለካከታቸውን ይገልጻሉ፣ ይደማመጣሉ። ሁልጊዜ ውሳኔ ላይ ላይደርስ ይችላል። ክርክር የሚያተኩረው የማን ሃሳብ ትክክል እንደሆነ ላይ ነው። የራስን አቋም በማስረጃ ለማስረዳት ይደረጋል፤ አንድ አሸናፊና አንድ ተሸናፊ ሊኖር ይችላል። ድርድር ደግሞ የጥቅም ግጭትን በመካከለኛ መፍትሔ ለመፍታት የሚደረግ ሂደት ነው። እያንዳንዱ ወገን ከአቋሙ በመቀነስ የጋራ መፍትሔ ለማግኘት ይሞክራል። ሀገራዊ ምክክር ግን ከእነዚህ ሁሉ የላቀ ሂደት ነው። ዓላማው ማንንም ማሸነፍ ወይም ማስሸነፍ ሳይሆን የሀገር የወደፊት አቅጣጫ ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። በምክክር ውስጥ የሚሸነፍ ሰው የለም፤ የሚያሸንፈው ሀገር ነው። የኢትዮጵያ ልዩ እውነታ፡- ኢትዮጵያ ሦስት ሺህ ዘመናትን የተሻገረ በሕብር ያሸበረቀ ታሪክ፣ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና ኃይማኖት ያላት ሀገር ናት። ይህ በሕብር ያሸበረቀ ልዩነት የኢትዮጵያ ጥንካሬ መሆን ሲገባው በተለያዩ ወቅቶች የፖለቲካ አለመግባባቶችና የታሪክ ትርክቶች የመከፋፈል መሣሪያ ሆነው ቆይተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ፈተናም ይህ ነው። ሁሉም የራሳቸውን ታሪክ ይዘው ወደ ጠረጴዛው ይመጣሉ፤ ነገር ግን ከጠረጴዛው የሚወጡት አንድ የጋራ የወደፊት ርዕይ ይዘው መሆን አለባቸው። ይህ ቀላል አይደለም። ስለዚህ ምክክሩ ከቃላት በላይ በተግባር የሚገለጥ ቅንነትን ይፈልጋል። የዋናው ምክክር ጉባኤ የህዝብ ወኪል ተመካካሪዎችም ሀገርን የማስቀደም ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ስኬታማ ምክክር የሚመሰረትባቸው አምስት ምሰሶዎች፡- ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን ቢያንስ አምስት መሠረታዊ ምሰሶዎች ሊኖሩት ይገባል። እነሱም መተማመን፣ አካታችነት፣ እውነት፣ ፍትሕና የጋራ ርዕይ ናቸው። ከሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበራሰብ የሕዝብ ወኪል 4 ሺ ተመካካሪ ኢትዮጵያዊያንም በሀገር ግንባታ ጉዳይ፣ የመንግስት አደረጃጃትና ስርአት ጉዳይ፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬድዋ ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና የመልካም አስተዳዳር ጉዳዮች፣ የሰላም ግንባታ ጉዳዮች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽ ማዕከል እየመከሩ ይገኛል። ሀገራዊ ምክክር ያለፈውን ለመቁጠር ሳይሆን፣ የወደፊቱን ለመገንባት የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው። የኢትዮጵያ መንገድም የልዩነት ግድግዳን የሚያፈርስ የትውልድ አደራና የብሔራዊ መግባባት ማሰሪያ ጥበብና ትልም ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፤ የተገኙ ዕድሎች፣ ዋና ፈተናዎች እና የወደፊት አቅጣጫ በታሪክ ጉዞዋ ውስጥ ኢትዮጵያ ብዙ የፈተና ዘመናትን አልፋለች። አንዳንዶቹ ፈተናዎች ከውጭ ጥቃት የመጡ ቢሆኑም፣ አብዛኞቹ ግን ከውስጣዊ አለመግባባቶች፣ ከተለያዩ የታሪክ ትርክቶች፣ ከፖለቲካ ፉክክርና ከመተማመን እጥረት የተፈጠሩ ናቸው። ስለዚህ የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት የዛሬን ችግር ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፣ የትውልድ ዕዳን ለማቃለል የተጀመረ ታሪካዊ ሂደት ነው። ይህ ሂደት ቀላል አይደለም። በርካታ ዓመታት የተከማቹ ቅሬታዎች፣ የተለያዩ እውነታዎች፣ የተቃራኒ ትርክቶችና የተለያዩ የፖለቲካ ፍላጎቶች በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መገናኘታቸው በራሱ ትልቅ ፈተና ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ ትልቁ ፈተና ልዩነትን ወደ መግባባት መቀየር ነው። ዕድሎች፤ ሊጠቀሙባቸው የሚገቡ ወሳኝ መስኮቶች፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ የምታነሳበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። የታሪክ አተረጓጎም፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የሥልጣን ክፍፍል፣ የሀብት አጠቃቀም፣ የፍትሕ ጉዳዮችና የአብሮነት ዕሴቶች በጦርነት ሳይሆን በሐሳብ የሚፈቱበት ዕድል ይፈጥራል። ከዚህም በላይ ምክክሩ የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር የሚያስችል ዕድል ነው። ለብዙ ዓመታት "አሸናፊና ተሸናፊ" በሚለው አስተሳሰብ የተመራውን ፖለቲካ ወደ "አብሮ ማሸነፍ" የሚሸጋግር ከሆነ እውነትም የኢትጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ ጠንካራ መሠረት ያገኛል። በሂደቱ ፊት የሚቆሙ ፈተናዎች፡- ማንኛውም ሀገራዊ ምክክር ከፍተኛ ተስፋ እንደሚፈጥር ሁሉ ከባድ ፈተናዎችንም ይዞ ይመጣል። የመጀመሪያው ፈተና የመተማመን እጥረት ነው። ለብዙ ዓመታት የተገነባ ጥርጣሬ በጥቂት ወራት አይጠፋም። ስለዚህ የምክክሩ ተዓማኒነት በእያንዳንዱ እርምጃ ሊገነባ ይገባል። ሁለተኛው ፈተና የተለያዩ የታሪክ ትርክቶች ናቸው። አንድ ክስተት በአንዱ ወገን የድል ታሪክ ሲሆን፣ በሌላው ወገን የመከራ ታሪክ ሊሆን ይችላል። ይህን ልዩነት በክብር መቀበል እንጂ መግፋት አይቻልም። በሌላ መልኩም የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ ስርጭት ነው። በዲጂታል ዘመን አንድ ያልተረጋገጠ መረጃ በጥቂት ደቂቃዎች ሺዎችን ሊደርስ ይችላል። ስለዚህ የሚዲያ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሚወስዱት ኃላፊነት ከመቼውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። የምሁራንና የመገናኛ ብዙኅን ሚና፡- በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ምሁራን ስሜትን ሳይሆን ማስረጃን ማቅረብ አለባቸው። የማኅበረሰብ ችግሮችን በሳይንሳዊ ጥናት መተንተን፣ ከሌሎች ሀገራት ልምድ መማርና አማራጭ መፍትሔዎችን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። መገናኛ ብዙኅንም በዚህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው። መገናኛ ብዙኅን ወሬን ከማባዛት ይልቅ እውነትን ማጣራት፣ ልዩነትን ከማባባስ ይልቅ መግባባትን ማጎልበት፣ ስሜትን ከማቀጣጠል ይልቅ እውነታን ማቅረብ አለበት። ምክክሩን የሚያጠናክር የመገናኛ አውታር ታሪክ ይሠራል፤ የሚያደናቅፍ ደግሞ በታሪክ ይጠየቃል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ቀን የሚጠናቀቅ ክስተት አይደለም። ምክክር በትውልድ የሚገነባ የፖለቲካ ባህል ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራውን ሊጨርስ ይችላል፤ ነገር ግን የመደማመጥ ባህል በሕዝብ ውስጥ ካልሰረጸ የምክክሩ እውነተኛ ዓላማ አይሳካም። የዛሬ ውሳኔ፤ የነገ ኢትዮጵያ፡- አንዳንድ የታሪክ ወቅቶች በየቀኑ አይመጡም። አንዳንድ ውሳኔዎችም የአንድ መንግሥት ዘመንን ብቻ ሳይሆን የትውልዶችን ዕጣ ፈንታ ይወስናሉ። ሀገራዊ ምክክር የእነዚህ ታሪካዊ ውሳኔዎች አንዱ ነው። ዛሬ በምንመርጠው የምክክር ባህል፣ በምንገነባው መተማመንና በምናሳየው የፖለቲካ ብስለት ላይ የነገዋን የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ተምሳሌት ኢትዮጵያ ያንፃል። ምክክር ሁሉንም ችግር በአንድ ጊዜ የሚፈታ አስማታዊ መፍትሔ አይደለም። ነገር ግን ጦርነትን ከውይይት፣ ጥላቻን ከመቻቻል፣ መከፋፈልን ከመተባበር የሚተካ ብልህ መንገድ ነው። የሚያደርገውም ልዩነቶችን ማጥፋት ሳይሆን ልዩነቶችን በአንድ ሀገር ጣሪያ ስር እንዴት እንደሚኖሩ የጋራ ሕግና ሥርዓት መፍጠር ነው። በእርግጥ ኢትዮጵያ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፋለች። የፖለቲካ አለመተማመን፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የፀጥታ ችግሮች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎችና የማኅበራዊ ስብራቶች በቀላሉ የሚያልፉ አይደሉም። ይሁን እንጂ እነዚህን ችግሮች በጥይት ከመፍታት ይልቅ በምክክር ለመፍታት መሞከር በራሱ የታሪክ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ ግን የአንድ ተቋም ብቻ አይደለም። የመንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኅን ተቋማት፣ የምሁራን፣ የወጣቶች፣ የሴቶችና የእያንዳንዱ ዜጋ የጋራ ኃላፊነት ነው። የሀገር ዕጣ ፋንታ ለአንድ ቡድን ብቻ የሚተው አይደለም፤ በጋራ የሚገነባ እንጂ። ከምክክር ወደ ባህል፡- ምክክሩ ተጠናቀቀ ማለት የሀገሪቱ ችግሮች ተፈቱ ማለት አይደለም። እውነተኛው ስኬት የሚለካው የመደማመጥ ባህል በማኅበረሰቡ ውስጥ ሲሰርጽ ነው። በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመገናኛ ብዙኅን፣ በፖለቲካ ተቋማትና በየቤቱ የመነጋገር ባህል ካልጠነከረ፣ ምክክሩ የሰነድ ውጤት ብቻ ሆኖ ይቀራል። የእውነተኛ ዴሞክራሲ መሠረት ተመሳሳይ አስተሳሰብ መኖር አይደለም፤ የተለያዩ አስተሳሰቦችን በሰላም የመቀበል ባህል መኖር ነው። ልዩነት የችግር ምንጭ ሳይሆን የጥንካሬ ምንጭ ሲሆን ነው አንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም የምታገኘው። የማጠቃለያ፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚያስፈልገው ብልህ አመራር ብቻ አይደለም፤ ታጋሽ ዜጎችንም ይፈልጋል። ሀገር የምትገነባው በግንብ ሳይሆን በመተማመን ነው። ሰላም የሚጸናውም በፍርሃት ሳይሆን በፍትሕ ነው። ዛሬ የምንመርጠው የምክክር መንገድ ነገ ለልጆቻችን የምንተወው ታሪክ ይሆናል። ስለዚህ በኢትዮጵያን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተደራጅተው የሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የዛሬ አጀንዳ ብቻ አይደሉም፤ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚቀርጽ የትውልድ አደራ እንጂ። የዋናው ምክክር ጉባኤ ተመካካሪ የሕዝብ ወኪሎችም ከግልና ቡድን ፍላጎት ይልቅ የቀጣዩን ትውልድና ሀገርን ማስቀደም ይጠበቅባቸውል። ምክክር የቃላት ልውውጥ ብቻ አይደለም፤ የተሰበረ መተማመንን የሚጠግን፣ የተከፋፈለ ማኅበረሰብን የሚያቀራርብ፣ የትውልድ ታሪክን በአዲስ ተስፋ የሚጽፍ ሀገራዊ ጥበብ ነው። የምንወስነው ዛሬ የምንወርሰውን ነገ ይበይናል። ምክክር የሀገር መድኅን ነው፤ ኢትዮጵያም እየመከረች ነው።
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 968
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 4933
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 11357
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 21283
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14310
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20062
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 67
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።
ዓይነ ስውሩ የቧንቧ ሰራተኛ
Jul 31, 2026 1089
ዋግ ኽምራ፤ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ) ፦"ዓይኖቼ ማየት ባይችሉም እጆቼ ተዓምር ይሰራሉ'' -ዓይነ ስውሩ የቧንቧ ሰራተኛ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ መለስ ጌታነህ የ62 ዓመት የእድሜ ባለጸጋ አዛውንት ናቸው፤ ከጊዜ በኋላ በመጣ ችግር የሁለት ዓይኖቻቸውን ብርሃን ያጡ ቢሆንም በአካባቢው ስመ ጥር የቧንቧ ሠራተኛ ናቸው። ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ ገና በወጣትነት ዕድሜያቸው የቧንቧ ሥራ ሙያን ቀስመው፣ በዋግ ኽምራ በሚገኙ ወረዳዎች በመንቀሳቀስ ለንጹሕ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት አሻራቸውን እያሳረፉ ያሉ ትጉህ ባለሙያ ናቸው። ቆላ በመውረድ፣ ደጋ በመውጣት፣ ተራራና ሸንተረሩን ሳይበግራቸው የውሃ መስመር በመዘርጋት ህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ እንዲደርሰው እያደረጉ ያሉ አዛውንት ናቸው። ለዚህም በተደጋጋሚ የምስጋና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በ1991 ዓ.ም የተፈራ ኃይሉ መታሰቢያ ጠቅላላ ሆስፒታል ሥራ ሲጀምር እሳቸው በቧንቧ ባለሙያነት በቋሚነት በመቀጠር፣ የውሃ መስመር በመዘርጋትና በመጠገን የሕክምና ክፍሎች ያልተቋረጠ ውሃ እንዲያገኙ ማድረግ ችለዋል። ይሁን እንጂ ከዕለታት በአንድ ቀን ሥራቸውን እያከናወኑ ባሉበት ወቅት ባላወቁት ምክንያት የሁለት ዓይኖቻቸውን ብርሃን ያጡበት አጋጣሚ በመከሰቱ ከቤት ለመዋል መገደዳቸውን ያወሳሉ። እንደ አቶ መለስ ገለጻ፡ “ዓይኔ ማየት ባለመቻሉ ራሴን ችዬ መንቀሳቀስ፣ እንደልቤ ሜትር ዘርግቼ ለክቼ መቁረጥና ገደል ላይ ተንጠልጥዬ የቧንቧ መስመር መዘርጋት አልችልም የሚል የተሸናፊነት ስሜት አድሮብኝ ተስፋ ቆርጬ ተቀምጬ ነበር” ይላሉ። በዚህ ወቅት ትጋታቸውንና ብርታታቸውን የሚያውቁ የሆስፒታሉ ዳይሬክተር የነበሩት ዶክተር ዓለማየሁ ትኩ፣ ወደ ሆስፒታሉ በመውሰድና በመምከር ሥራቸውን እንዲቀጥሉ እንዳገዟቸው አውስተዋል። ቀስ በቀስም አቶ መለስ ሜትር በመዘርጋትና መጋዝ በመጨበጥ ልኬታን አስተካክለው፣ መገጣጠሚያ ቦታዎችን በዳበሳ ለይተው የቧንቧ ሙያ ሥራቸውን እንደገና “ሀ” ብለው ማስቀጠላቸውን አመልክተዋል። ምንም እንኳን ከወረዳ ወረዳ ተንቀሳቅሶ መሥራት ባይችሉም፣ በግለሰብ ቤቶችና ድርጅቶች እየተንቀሳቀሱ የቧንቧ ጥገና ሥራቸውን በብቃት እያከናወኑ ያሉ ብቁ ባለሙያ ሆነው ቀጥለዋል። በሆስፒታሉም ከአገልግሎት ውጭ የነበሩ የውሃ መስመሮችን በመለየትና በአግባቡ በመጠገን፣ ለሐኪሞችና ለሕመምተኞች ወጥ የሆነ የንጹሕ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ “አንቱ” የተባሉ ባለሙያ ሆነዋል። አቶ መለስ በቧንቧ ሥራ ሳይገደቡ፣ በራዲዮ በሚቀርቡ የቴክኖሎጂ ፕሮግራሞች ባገኙት እውቀት ከአገልግሎት ውጭ የነበረውን የሆስፒታሉን የላውንድሪ (ልብስ ማጠቢያ) ማሽን በዳበሳ ጠግነው ወደ አገልግሎት በመመለስ ሆስፒታሉን ከወጪ ታድገዋል። “ብርሃን ከዓይን ብቻ ሳይሆን ከልብና ከመዳፋችንም ይገኛል” የሚሉት አቶ መለስ፣ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ምጣዶችን በመጠገንና ሌሎችንም የቴክኒክ ሥራዎች በመሥራት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን የሚያስተዳድሩ ጠንካራ የዕድሜ ባለፀጋ ናቸው። "የዓይን ብርሃኔን አጣሁ ብዬ አንድም ቀን አስቤ አላውቅም” የሚሉት አቶ መለስ፣ አሁን ላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ጣራ ላይ በመውጣት ጭምር ቧንቧ ጠግነው የሚወርዱ ባለሙያ ሆነዋል። “እኔ ሥራ ሳልሠራ ስውል ያመኛል” የሚሉት አቶ መለስ፣ ወጣቱ ሥራን ሳይንቅ ከሰራ ከትንሽ ነገር ተነስቶ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም ትልቅ ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚችል ምክራቸውን ለግሰዋል። ስለ ጉዳዩ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተፈራ ኃይሉ ጠቅላላ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምሩ ቢምረው እንዳሉት፡ ጋሽ መለስ የዓይን ብርሃናቸውን ቢያጡም በሙያቸው የትጋትና የ“ይቻላል” ተምሳሌት የሆኑ አዛውንት ናቸው። አዛውንቱ በሙያቸው የሆስፒታሉ የውሃ አቅርቦት እንዳይቋረጥ በማድረግ ለሕክምና ሥራ መቀላጠፍ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸው ለሌሎች ባለሙያዎች በታታሪነት፣ በሥራ ፍቅር እና በጥንካሬ አርዓያ መሆናቸውንም ገልጸዋል።