ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ጉልህ ድርሻ ያበረክታሉ
Jun 30, 2026 22
ሐረር፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩት አጀንዳዎች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ያላቸው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን በሐረር የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረጋቸው ተከታታይ ውይይቶች፤ ለዘመናት የቆዩ መዋቅራዊ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ይህንኑ አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሐረር ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች፤ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው የተለዩት አጀንዳዎች ወቅታዊና ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሐረሪ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች ጥምረት ሰብሳቢ አቶ መሐመድ ዩሱፍ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ከጥምረቱ ጋር በቅንጅት እየሠራ ሲሆን፣ እስካሁን ባለው ሂደትም አበረታች ተግባራትን አከናውኗል። ኮሚሽኑ የለያቸው አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ለመገንባትና ለዘመናት ሳያግባቡ የቆዩ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሀገር ሽማግሌው አቶ መሀመድ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ያሉ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የሀገራዊ ምክክሩ ሚና ከፍተኛ ነው። በመሆኑም ለዚህ ሂደት ስኬታማነት ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽኦ ማበርከት ይገባናል ብለዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የማያግባቡ ጉዳዮችን በውይይት ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፤ ጠንካራ ሥርዓተ-መንግስት ለመገንባት፣ የጋራ ትርክትን ለማስረጽና ዴሞክራሲን ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው የገለጹት ደግሞ አባገዳ አህመድ ዩስፍ ናቸው። ኮሚሽኑ ሰሞኑን ይፋ ያደረገው አጀንዳ በሀገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍና ልዩነቶችን ወደ ትብብር በመቀየር ዘላቂ ሰላምን እንደሚያሰፍን ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።   በክልሉ የጀንኤላ ወረዳ የሰላም ቤተሰብ ሰብሳቢ መምህርት ሒሩት ታደሰ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በሀገሪቱ የነበሩ አለመግባባቶችን እስከ ታችኛው የህብረተሰብ ክፍል በመውረድ ለመፍታትና ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት እያከናወነ የሚገኘውን ተግባር አድንቀዋል። ኮሚሽኑ አጀንዳዎችን ለይቶ ወደ ስራ መግባቱ ኢትዮጵያን ወደ አንድነት የሚያመጣ፣ ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍንና ጠንካራ ሀገረ-መንግስት ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህንን ታሪካዊ ዕድል በመጠቀም ሰላማዊና የተሻለች ሀገር ለመገንባት እያበረከቱ የሚገኘውን አስተዋጽኦ ይበልጥ እንደሚያጠናክሩም አክለው ገልጸዋል።
በከተማዋ ተገንብቶ ወደ ስራ የገባው መናኸሪያ የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር አስችሏል
Jun 30, 2026 33
ሚዛን አማን፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሚዛን አማን ከተማ ተገንብቶ ወደ ስራ የገባው አዲሱ መናኸሪያ የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር ምቹ ሁኔታን መፍጠሩን አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎች ገለጹ። በቅርቡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሚዛን አማን ከተማ የተገነባው አዲስ መናኸሪያ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ይታወሳል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የመናኸሪያው ተገልጋዮች እንደገለፁት፤ አዲሱ መናኸሪያ ከዚህ ቀደም የነበረውን የመጥበብና የንጽህና ጉድለት ችግር በማስቀረት የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር አስችሏል። ይህም መንግስት ሕዝብን ለእንግልት ይዳርጉ የነበሩ የመሠረተ ልማት ክፍተቶችን ለይቶ በማዘመን ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ መሆኑን የሚያመላክት እንደሆነም ተናግረዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል በዛብህ በቀለ እና አብዮት ወልደማርያም፤ ከዚህ ቀደም የነበረው መናኸሪያ ጠባብ በመሆኑ ቶሎ ስለሚሞላ አገልግሎት የሚሰጡበትን ተሽከርካሪ ውጭ ለማሳደር ይገደዱ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህም ለተሽከርካሪዎች ደህንነት ምቹ እንዳልነበር በማንሳት የእቃ መጥፋትና ለፓርኪንግ ወጪ የማውጣት ጫና ፈጥሮብን ቆይቷል አሁን ግን ይህ ችግር ተቀርፎልናል ብለዋል። አዲሱ መናኸሪያ በአግባቡ ተጠብቆ እንዲዘልቅ የበኩላችንን ኃላፊነት እንወጣለን ብለዋል።   ከተሳፋሪዎች መካከል ወይዘሮ ዓለሚቱ ገረመው እና ታደለ ኃይለኢየሱስ፤ አዲሱ መናኸሪያ የተሻለ በመሆኑ ደህንነታቸው ተጠብቆ በሥነ ሥርዓት አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል። ቀደም ሲል በዝናብ ጊዜ በሚፈጠረው ጭቃ ምክንያት ለመውጣትና መግባት እንኳ ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰው መንግስት ደረጃውን የጠበቀ ግንባታ በማከናወን ለችግሩ መፍትሔ በመስጠቱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘመዴ አንዳርጌ፤ በክልሉ የሚታዩ የመናኸሪያ አገልግሎት ችግሮችን ለመቅረፍ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።   ከ425 በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግደው የሚዛን አማን መናኸሪያ በውስጡ የትራንስፖርት ማኅበራት ቢሮ፣ የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት፤ ካፍቴሪያና ሌሎች ክፍሎችንም ያሟላ ነው ብለዋል። ለግንባታው ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸው ለተሳፋሪዎች ምቹ ማረፊያና ሰፊ መንቀሳቀሻ እንዲኖረው ተደርጎ መሰራቱን ጠቁመዋል። በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ መናኸሪያዎች በዲጂታል ሲስተም ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን በቅርቡ የተመረቀውን የታርጫና በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የቦንጋ መናኸሪያዎች ለአብነት ጠቅሰዋል።
በቱሪዝም ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት የሀገርን ኢኮኖሚና ገጽታ ለመገንባት የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ
Jun 30, 2026 90
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በቱሪዝም ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት የሀገርን ኢኮኖሚና ገጽታ ለመገንባት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ። የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩት “የላቀ ክህሎት ለቱሪዝም እድገት” በሚል መሪ ቃል 13ኛውን የቱሪዝምና የመስተንግዶ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር ጀምሯል።   በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ፣ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ተዋናዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ መንግሥት በቱሪዝም ዘርፉ ውጤታማና ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። ይህንን ማሻሻያ ተከትሎም የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩትን የማጠናከር ሥራ የተሠራ ሲሆን፣ ተቋሙ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የቱሪዝም መስኮች ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ማፍራት መቻሉን ጠቁመዋል። ኢንስቲትዩቱ ከመደበኛ ትምህርት በተጨማሪ አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት ለበርካታ ዜጎች መድረስ መቻሉን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በዚህም ለብዙዎች የሥራ ዕድል እየተፈጠረ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዘርፉ ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለውጭ ሀገራት ገበያም ተወዳዳሪ መሆን የሚችል የሰው ኃይል እየፈራ ይገኛል፤ ይህ ተግባር ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። ቱሪዝም ካለው ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ባሻገር ለሀገር ገጽታ ግንባታ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው በቀጣይም የአገልግሎት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ በልዩ ትኩረት መሥራት ይገባል ብለዋል። የቱሪዝምና መስተንግዶ ሳምንት መከበሩ፣ የሥራ ገበያውንና የሰለጠነውን የሰው ኃይል በቀጥታ ለማገናኘት እንዲሁም ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዱ ጠቃሚ ግብዓቶችን ለመሰብሰብ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።   የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ በበኩላቸው፤ ተቋሙ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን በማፍራት ለኢንዱስትሪው ዕድገት የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝና በቀጣይም ይህንን ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የዘንድሮው የቱሪዝምና መስተንግዶ ሳምንትም ኢንስቲትዩቱን ይበልጥ ውጤታማ ሊያደርጉ በሚችሉና ዘርፉን በሚያሳድጉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር ገልጸዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት የሀገርን ዕድገትና ብልፅግና የሚያፋጥኑ ተግባራት ላይ ትኩረት ሊያደርግ ይገባል
Jun 30, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሰረት የሚመሰረተው አዲስ መንግሥት የሀገርን ዕድገትና ብልፅግና ለሚያፋጥኑ የልማት ስራዎች ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ምሁራን ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ብልፅግና ፓርቲ መንግሥት ለመመስረት የሚያስችለውን አብላጫ ድምፅ አግኝቷል፡፡ በመሆኑም አሸናፊው ብልፅግና ፓርቲ በመጪው መስከረም ወር ላይ አዲስ መንግሥት የሚመሰርት ይሆናል፡፡ አዲስ የሚመሰረተውን መንግሥት በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን፥ አዲሱ መንግሥት ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ፣ አብሮነትና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር ላይ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል ብለዋል። ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የሀገር ዕድገትና ብልፅግናን የሚያፋጥኑ ተግባራትን በስኬት ማከናወን እንዳለበትም ነው ያነሱት። በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የስነ መንግሥትና ሕዝብ አስተዳደር ተመራማሪና ተንታኝ ጫሊ ኢተፋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ምርጫ ሕዝብ ድምፅ ለሰጠው ፓርቲ አደራና ኃላፊነት የሚያስረክብበት የዴሞክራሲ ሂደት ነው። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መካሄዱን ጠቅሰው፥ በምርጫው ውጤት መሰረት አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት የተጀመሩ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳሩን የማስፋት ስራዎች ማስቀጠል አለበት ብለዋል። የትኛውም ሀገራዊ ችግር በምክክርና በውይይት ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኝ በሆደ ሰፊነት መሥራት እንዳለበትም ጠቁመዋል። በተጨማሪም ለመልካም አስተዳደርና ለሀገር እድገት ማነቆ የሆኑ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን የሚያስቀሩ ፖሊሲዎችና አሰራሮችን በተደራጀ መልኩ መተግበር ይጠበቅበታል ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት በሚል መርህ እየተከተለች ያለው ቀጣናዊ ትስስርን የማጠናከር የመሪነት ሚናዋን ማስቀጠልም አለበት ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰላምና ደህንነት መምህርና ተመራማሪ ሙሉጌታ አየለ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በቀጣይ የሚመሰረተው መንግሥት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ዘርፉን ይበልጥ በማዘመን ብልሹ አሠራርን ማስቀረት ቀዳሚ የቤት ሥራው ሊሆን እንደሚገባ አንስተዋል። ለዚህም የተጀመረው የጠንካራ ተቋማት ግንባታ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ነው የተናገሩት። የሥራ ዕድል የሚፈጥሩና የሉዓላዊነት ቁልፍ አጀንዳ የሆነውን በምግብ ራስን የመቻል ግብን የሚያረጋግጡ የፖሊሲ ትግበራዎችን ማጠናከር ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ ሥራዎች ናቸው ብለዋል።
መገናኛ ብዙሃን ለስርዓተ ጾታ እኩልነት ይበልጥ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል
Jun 30, 2026 110
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ለስርዓተ ጾታ እኩልነት ይበልጥ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ ገለጹ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ከኢንተርናሽናል ሚዲያ ስፖርት (IMS) ጋር በመተባበር፤ በስርዓተ ጾታ እና የሴት ጋዜጠኞችን ማብቃት ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት እያካሄደ ይገኛል።   በዚህ መድረክ ላይ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ድርጅቶች የተወጣጡ ሴት ጋዜጠኞች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው። ዋና ዳይሬክተሯ ሃይማኖት በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ መገናኛ ብዙኃን የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማስፈን ለሚከናወኑ ተግባራት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል። በተለይም ሴቶች በህብረተሰቡ ውስጥ ያላቸውን ጉልህ ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት፣ በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ በአመራርነትና በውሳኔ ሰጪነት ደረጃ ሊጎለብት እንደሚገባ አሳስበዋል። የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 ሴቶች የሕብረተሰቡ ግማሽ አካል እንደመሆናቸው መጠን እንደ የዕድሜያቸውና እንደ የስርዓተ-ፆታ ፍላጎታቸዉ፣ ተግዳሮቶቻቸውንና እምቅ አቅማቸዉን የሚመጥኑ ፕሮግራሞች ሊዘጋጁላቸው እንደሚገባ ይደነግጋል ብለዋል። ሴቶች በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ንቁ ተጠቃሚና ውሳኔ ሰጪ እንዲሆኑ የሚያስገድዱ ጠንካራ መርሆዎች መኖር እንዳለባቸውም በአዋጁ መደንገጉን ጠቅሰዋል፡፡ በማንኛውም የመገናኛ ብዙኃን ውጤት ሴቶችን ዝቅ አድርጎ የማቅረብ አዝማሚያ በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፤ የሴቶችን ክብርና እኩልነት የመጠበቅ የሕግ ግዴታም መጣሉን ነው የገለጹት፡፡ በተጨማሪም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ ደረጃ የሴቶችን መብት፣ ውክልናና ተሳትፎ ለማጠናከር በርካታ ስምምነቶችን ተቀብላ እየተገበረች መሆኑን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት በብዙ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ውስጥ በአመራር ደረጃ፣ በውሳኔ ሰጪነት እና በይዘት ዝግጅት ሂደት ላይ የሴቶች ተሳትፎ መሻሻሎችን እያሳየ ቢሆንም ይበልጥ ሊጎለብት ይገባል ብለዋል፡፡   ይህንን ለማቃለል በመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ውስጥ ጠንካራ የስርዓተ ጾታ ምላሽ ሰጪ የመገናኛ ብዙኃን ፖሊሲዎችን፣ የሴት ባለሙያዎችን የሥራ አካባቢ ደህንነት የሚያረጋግጡ መመሪያዎችን እና ግልጽ የክትትልና የተጠያቂነት አሰራር መዘርጋት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። በቀጣይም የሴቶችን ተሳትፎና አመራር ሰጪነት ማጠናከር፣ በይዘት ምርትና ስርጭት ሂደት የስርዓተ ጾታ ሚዛንን ማረጋገጥ፣ ከፆታዊ ትንኮሳ ነፃ የሆነ ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር፣ የሚዲያ ይዘቶችን በስርዓተ ጾታ መነፅር መከታተል፣ አግላይና አድሎአዊ የሆኑ ቋንቋዎችን ማስወገድ፣ ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታና ሥልጠና ሥርዓት ማበጀት ይገባል ብለዋል። መገናኛ ብዙኃን የተጠናከረ የስርዓተ ፆታ ኤዲቶሪያል አሰራር በመዘርጋት፣ ለስርዓተ ፆታ ጉዳዮች በቂ የአየር ሰዓትና ሽፋን በመስጠት፣ ሕግና የሙያውን ሥነ-ምግባር አክብረው የሚያቀርቡበትን አሠራር መዘርጋት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ በአጽንኦት አሳስበዋል።
የሚታይ
በቱሪዝም ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት የሀገርን ኢኮኖሚና ገጽታ ለመገንባት የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ
Jun 30, 2026 90
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በቱሪዝም ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት የሀገርን ኢኮኖሚና ገጽታ ለመገንባት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ። የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩት “የላቀ ክህሎት ለቱሪዝም እድገት” በሚል መሪ ቃል 13ኛውን የቱሪዝምና የመስተንግዶ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር ጀምሯል።   በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ፣ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ተዋናዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ መንግሥት በቱሪዝም ዘርፉ ውጤታማና ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። ይህንን ማሻሻያ ተከትሎም የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩትን የማጠናከር ሥራ የተሠራ ሲሆን፣ ተቋሙ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የቱሪዝም መስኮች ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ማፍራት መቻሉን ጠቁመዋል። ኢንስቲትዩቱ ከመደበኛ ትምህርት በተጨማሪ አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት ለበርካታ ዜጎች መድረስ መቻሉን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በዚህም ለብዙዎች የሥራ ዕድል እየተፈጠረ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዘርፉ ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለውጭ ሀገራት ገበያም ተወዳዳሪ መሆን የሚችል የሰው ኃይል እየፈራ ይገኛል፤ ይህ ተግባር ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። ቱሪዝም ካለው ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ባሻገር ለሀገር ገጽታ ግንባታ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው በቀጣይም የአገልግሎት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ በልዩ ትኩረት መሥራት ይገባል ብለዋል። የቱሪዝምና መስተንግዶ ሳምንት መከበሩ፣ የሥራ ገበያውንና የሰለጠነውን የሰው ኃይል በቀጥታ ለማገናኘት እንዲሁም ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዱ ጠቃሚ ግብዓቶችን ለመሰብሰብ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።   የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ በበኩላቸው፤ ተቋሙ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን በማፍራት ለኢንዱስትሪው ዕድገት የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝና በቀጣይም ይህንን ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የዘንድሮው የቱሪዝምና መስተንግዶ ሳምንትም ኢንስቲትዩቱን ይበልጥ ውጤታማ ሊያደርጉ በሚችሉና ዘርፉን በሚያሳድጉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር ገልጸዋል።
መገናኛ ብዙሃን ለስርዓተ ጾታ እኩልነት ይበልጥ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል
Jun 30, 2026 110
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ለስርዓተ ጾታ እኩልነት ይበልጥ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ ገለጹ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ከኢንተርናሽናል ሚዲያ ስፖርት (IMS) ጋር በመተባበር፤ በስርዓተ ጾታ እና የሴት ጋዜጠኞችን ማብቃት ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት እያካሄደ ይገኛል።   በዚህ መድረክ ላይ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ድርጅቶች የተወጣጡ ሴት ጋዜጠኞች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው። ዋና ዳይሬክተሯ ሃይማኖት በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ መገናኛ ብዙኃን የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማስፈን ለሚከናወኑ ተግባራት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል። በተለይም ሴቶች በህብረተሰቡ ውስጥ ያላቸውን ጉልህ ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት፣ በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ በአመራርነትና በውሳኔ ሰጪነት ደረጃ ሊጎለብት እንደሚገባ አሳስበዋል። የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 ሴቶች የሕብረተሰቡ ግማሽ አካል እንደመሆናቸው መጠን እንደ የዕድሜያቸውና እንደ የስርዓተ-ፆታ ፍላጎታቸዉ፣ ተግዳሮቶቻቸውንና እምቅ አቅማቸዉን የሚመጥኑ ፕሮግራሞች ሊዘጋጁላቸው እንደሚገባ ይደነግጋል ብለዋል። ሴቶች በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ንቁ ተጠቃሚና ውሳኔ ሰጪ እንዲሆኑ የሚያስገድዱ ጠንካራ መርሆዎች መኖር እንዳለባቸውም በአዋጁ መደንገጉን ጠቅሰዋል፡፡ በማንኛውም የመገናኛ ብዙኃን ውጤት ሴቶችን ዝቅ አድርጎ የማቅረብ አዝማሚያ በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፤ የሴቶችን ክብርና እኩልነት የመጠበቅ የሕግ ግዴታም መጣሉን ነው የገለጹት፡፡ በተጨማሪም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ ደረጃ የሴቶችን መብት፣ ውክልናና ተሳትፎ ለማጠናከር በርካታ ስምምነቶችን ተቀብላ እየተገበረች መሆኑን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት በብዙ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ውስጥ በአመራር ደረጃ፣ በውሳኔ ሰጪነት እና በይዘት ዝግጅት ሂደት ላይ የሴቶች ተሳትፎ መሻሻሎችን እያሳየ ቢሆንም ይበልጥ ሊጎለብት ይገባል ብለዋል፡፡   ይህንን ለማቃለል በመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ውስጥ ጠንካራ የስርዓተ ጾታ ምላሽ ሰጪ የመገናኛ ብዙኃን ፖሊሲዎችን፣ የሴት ባለሙያዎችን የሥራ አካባቢ ደህንነት የሚያረጋግጡ መመሪያዎችን እና ግልጽ የክትትልና የተጠያቂነት አሰራር መዘርጋት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። በቀጣይም የሴቶችን ተሳትፎና አመራር ሰጪነት ማጠናከር፣ በይዘት ምርትና ስርጭት ሂደት የስርዓተ ጾታ ሚዛንን ማረጋገጥ፣ ከፆታዊ ትንኮሳ ነፃ የሆነ ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር፣ የሚዲያ ይዘቶችን በስርዓተ ጾታ መነፅር መከታተል፣ አግላይና አድሎአዊ የሆኑ ቋንቋዎችን ማስወገድ፣ ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታና ሥልጠና ሥርዓት ማበጀት ይገባል ብለዋል። መገናኛ ብዙኃን የተጠናከረ የስርዓተ ፆታ ኤዲቶሪያል አሰራር በመዘርጋት፣ ለስርዓተ ፆታ ጉዳዮች በቂ የአየር ሰዓትና ሽፋን በመስጠት፣ ሕግና የሙያውን ሥነ-ምግባር አክብረው የሚያቀርቡበትን አሠራር መዘርጋት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ በአጽንኦት አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለዓለም ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራዊ እርምጃዎቿን አጠናክራ ትቀጥላለች 
Jun 30, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለዓለም ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራዊ እርምጃዎቿን አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡን ያሳተፈው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በእንጦጦ ፓርክ በተካሄደው በዚህ መርሃ ግብር ላይ የየሀገራቱ አምባሳደሮች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ለዓለም ምሳሌ በሚሆን መልኩ በውጤታማነት እየተገበረች ትገኛለች።   መርሃ ግብሩ የተጎዱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ ከማድረግ ባለፈ፣ በስራ ዕድል ፈጠራና ዘላቂ ልማትን እውን በማድረግ ረገድ ተጠቃሽ ውጤቶች እያመጣ መሆኑንም አብራርተዋል። የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ የአረንጓዴ አሻራ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ፤ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ረገድ የምትጫወተውን ግንባር ቀደም ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። የአየር ንብረት ለውጥ አንድ ሀገር ብቻውን መፍትሔ ሊሰጠው የሚችለው ጉዳይ ባለመሆኑ በጋራ መስራት ወሳኝ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ የዛሬው የችግኝ ተከላም ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ለዱር እንስሳት ህልውና ዓይነተኛ ሚና እንዳለው አንስተዋል። ዛሬ የምንተክለው ችግኝ ብቻ ሳይሆን ለመጪው ትውልድ ተስፋም ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የመሬት አካውንት መግለጫና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታ ይፋ ሆነ
Jun 30, 2026 178
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው፣ አካታችና የማይበገር ዕድገት ለማስመዝገብ ለምታደርገው ጥረት ጠቃሚ መሰረት ሆኖ የሚያገለግለው የመሬት አካውንት መግለጫና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታ ይፋ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዕትም የመሬት አካውንት መግለጫ ሪፖርት እና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታን ይፋ የማድረጊያ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል። በዚህ ይፋዊ መድረክ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍስሃፅዮን፣ የዓለም ባንክ የኦፕሬሽን ማናጀር ጁልያን ቪክቶር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍሰሃፅዮን በመድረኩ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፤ ይፋ የሆኑት ሰነዶች ሀገራዊ የጋራ ራዕይን እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም አላቸው። በተለይም በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ለመቅረጽ፣ የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል፣ ቀጣይነት ያለው ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጋራ ለመስራት ያለንን ቁርጠኝነት የምናሳይበት ነው ብለዋል።   እነዚህ ሰነዶች ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት በተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች የተዘጋጁ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህም የላቀ የትብብር ውጤት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። ሰነዶቹ የተዘጋጁት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር በሚመራው ስቲሪንግ ኮሚቴ፣ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ተቋማት የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሆነም አክለዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በአህጉሪቱ ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት የቻለች ብሎም የሚጨበጥ ስኬት ያስመዘገበች ሀገር መሆኗንም ጠቅሰዋል፡፡ ይህ ያስመዘገበችው ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገትም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ህይወት በተጨባጭ መለወጡን ጠቁመዋል። ለዚህ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ስኬት ለመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ለጤና እና ለትምህርት የተሰጠው ከፍተኛ ትኩረትና በሌሎችም የተደረገው ኢንቨስትመንት ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷልም ብለዋል። ቀጣይነት ያለውን ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተፈጥሮ ሀብቶችን የመጠበቅ፣ የመንከባከብና የማልማት ተግባራትም በተሳካ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ይወስዳሉ
Jun 30, 2026 193
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና እንደሚወስዱ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በአብርሆት ቤተመጸሐፍት ተገኝተው የፈተናውን ሂደት አስጀምረዋል።   የፈተናውን ሂደት አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኅን በሰጡት መግለጫም፤ ፈተናው በበይነመረብና በወረቀት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል። የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሚወስዱት አጠቃላይ ተፈታኝ ተማሪዎች ውስጥ 62 በመቶ የሚሆኑ በበይነ መረብ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ በወረቀት እንደሚወስዱ ገልጸዋል።   በዘንድሮው ዓመት ከፍተኛ የማጠናከሪያ ትምህርት በመሰጠቱ ከፍ ያለ ውጤት ይመዘገባል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል። የዘንድሮው ፈተና ያለምንም ሥርቆት ተማሪዎች በችሎታቸውና በብቃታቸው የሚፈተኑት መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱም አስታውቀዋል።   የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር)፤ በከተማዋ 58 ሺህ 309 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል። በአዲስ አበባም የመልቀቂያ ፈተናው በአጠቃላይ ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ጉልህ ድርሻ ያበረክታሉ
Jun 30, 2026 22
ሐረር፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩት አጀንዳዎች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ያላቸው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን በሐረር የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረጋቸው ተከታታይ ውይይቶች፤ ለዘመናት የቆዩ መዋቅራዊ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ይህንኑ አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሐረር ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች፤ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው የተለዩት አጀንዳዎች ወቅታዊና ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሐረሪ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች ጥምረት ሰብሳቢ አቶ መሐመድ ዩሱፍ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ከጥምረቱ ጋር በቅንጅት እየሠራ ሲሆን፣ እስካሁን ባለው ሂደትም አበረታች ተግባራትን አከናውኗል። ኮሚሽኑ የለያቸው አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ለመገንባትና ለዘመናት ሳያግባቡ የቆዩ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሀገር ሽማግሌው አቶ መሀመድ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ያሉ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የሀገራዊ ምክክሩ ሚና ከፍተኛ ነው። በመሆኑም ለዚህ ሂደት ስኬታማነት ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽኦ ማበርከት ይገባናል ብለዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የማያግባቡ ጉዳዮችን በውይይት ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፤ ጠንካራ ሥርዓተ-መንግስት ለመገንባት፣ የጋራ ትርክትን ለማስረጽና ዴሞክራሲን ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው የገለጹት ደግሞ አባገዳ አህመድ ዩስፍ ናቸው። ኮሚሽኑ ሰሞኑን ይፋ ያደረገው አጀንዳ በሀገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍና ልዩነቶችን ወደ ትብብር በመቀየር ዘላቂ ሰላምን እንደሚያሰፍን ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።   በክልሉ የጀንኤላ ወረዳ የሰላም ቤተሰብ ሰብሳቢ መምህርት ሒሩት ታደሰ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በሀገሪቱ የነበሩ አለመግባባቶችን እስከ ታችኛው የህብረተሰብ ክፍል በመውረድ ለመፍታትና ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት እያከናወነ የሚገኘውን ተግባር አድንቀዋል። ኮሚሽኑ አጀንዳዎችን ለይቶ ወደ ስራ መግባቱ ኢትዮጵያን ወደ አንድነት የሚያመጣ፣ ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍንና ጠንካራ ሀገረ-መንግስት ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህንን ታሪካዊ ዕድል በመጠቀም ሰላማዊና የተሻለች ሀገር ለመገንባት እያበረከቱ የሚገኘውን አስተዋጽኦ ይበልጥ እንደሚያጠናክሩም አክለው ገልጸዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት የሀገርን ዕድገትና ብልፅግና የሚያፋጥኑ ተግባራት ላይ ትኩረት ሊያደርግ ይገባል
Jun 30, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሰረት የሚመሰረተው አዲስ መንግሥት የሀገርን ዕድገትና ብልፅግና ለሚያፋጥኑ የልማት ስራዎች ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ምሁራን ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ብልፅግና ፓርቲ መንግሥት ለመመስረት የሚያስችለውን አብላጫ ድምፅ አግኝቷል፡፡ በመሆኑም አሸናፊው ብልፅግና ፓርቲ በመጪው መስከረም ወር ላይ አዲስ መንግሥት የሚመሰርት ይሆናል፡፡ አዲስ የሚመሰረተውን መንግሥት በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን፥ አዲሱ መንግሥት ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ፣ አብሮነትና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር ላይ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል ብለዋል። ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የሀገር ዕድገትና ብልፅግናን የሚያፋጥኑ ተግባራትን በስኬት ማከናወን እንዳለበትም ነው ያነሱት። በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የስነ መንግሥትና ሕዝብ አስተዳደር ተመራማሪና ተንታኝ ጫሊ ኢተፋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ምርጫ ሕዝብ ድምፅ ለሰጠው ፓርቲ አደራና ኃላፊነት የሚያስረክብበት የዴሞክራሲ ሂደት ነው። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መካሄዱን ጠቅሰው፥ በምርጫው ውጤት መሰረት አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት የተጀመሩ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳሩን የማስፋት ስራዎች ማስቀጠል አለበት ብለዋል። የትኛውም ሀገራዊ ችግር በምክክርና በውይይት ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኝ በሆደ ሰፊነት መሥራት እንዳለበትም ጠቁመዋል። በተጨማሪም ለመልካም አስተዳደርና ለሀገር እድገት ማነቆ የሆኑ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን የሚያስቀሩ ፖሊሲዎችና አሰራሮችን በተደራጀ መልኩ መተግበር ይጠበቅበታል ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት በሚል መርህ እየተከተለች ያለው ቀጣናዊ ትስስርን የማጠናከር የመሪነት ሚናዋን ማስቀጠልም አለበት ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰላምና ደህንነት መምህርና ተመራማሪ ሙሉጌታ አየለ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በቀጣይ የሚመሰረተው መንግሥት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ዘርፉን ይበልጥ በማዘመን ብልሹ አሠራርን ማስቀረት ቀዳሚ የቤት ሥራው ሊሆን እንደሚገባ አንስተዋል። ለዚህም የተጀመረው የጠንካራ ተቋማት ግንባታ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ነው የተናገሩት። የሥራ ዕድል የሚፈጥሩና የሉዓላዊነት ቁልፍ አጀንዳ የሆነውን በምግብ ራስን የመቻል ግብን የሚያረጋግጡ የፖሊሲ ትግበራዎችን ማጠናከር ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ ሥራዎች ናቸው ብለዋል።
አዲስ የሚዋቀረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገራዊ ለውጡ የፈጠረውን የብልፅግና ጉዞ የማስቀጠል የህዝብ አደራ አለበት
Jun 30, 2026 166
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሰረት የሚዋቀረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ የፈጠረውን የብልፅግና ጉዞ የማስቀጠል የህዝብ አደራ እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሁሉን አቀፍ፣ ነፃ፣ ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ በሆነና ድምፅ በሚስጥር በሚሰጥበት ሥርዓት በየአምስት ዓመቱ በሕዝብ እንደሚመረጡ በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥቱ አንቀፅ-54 ላይ በግልፅ ተመላክቷል። የምክር ቤቱ አባላትም የመላው ሕዝብ ተወካዮች በመሆናቸው ተገዥነታቸው ለሕገ-መንግሥቱ፣ ለሕዝቡና ለሕሊናቸው ብቻ መሆኑን በሕዝብ ውክልና የክትትልና ቁጥጥር ኃላፊነት እንደተሰጣቸው ተቀምጧል። በሕገ-መንግሥት አንቀፅ-58 መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚመረጠው ለአምስት ዓመታት ነው፤ የሥራ ዘመኑም ከማብቃቱ አንድ ወር በፊት አዲስ ምርጫ ተካሂዶ ይጠናቀቃል። ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎም በመጪው መስከረም ወር አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ አዲስ መንግሥት እንደሚመሰርት ይጠበቃል። ስድስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመንም በዚህ ዓመት የሚጠናቀቅ ሲሆን፤ በመጪው መስከረም አዲሱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚቋቋም ይሆናል። በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጀ እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎችን የልማት፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ጽኑ ፍላጎት አስመስክሯል። ሕብረተሰቡ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ጭምር በመሰለፍ ይወክለኛል ለሚለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ መስጠቱም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየቱን ገልጸዋል። በጠቅላላ ምርጫው ውጤት መሰረት የሚዋቀረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ የፈጠረውን የብልፅግና ጉዞ የማስቀጠል የህዝብ አደራ እንዳለበት ተናግረዋል። በቀጣይ መስከረም በይፋ ሥራውን የሚጀምረው አዲሱ ምክር ቤትም የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች የሚያፋጥን ጥብቅ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ እንደሚጠበቅበት አንስተዋል። በተለይም ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች በስኬት ተጠናቀው የሀገርና ህዝብ ሁለንተናዊ የዕድገት አቅም እንዲሆኑ የማድረግ ታሪካዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደሚጠይቅ አስረድተዋል። በምክር ቤቱ የጤና፣ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ በርካታ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ነው ብለዋል። አዲሱ ምክር ቤትም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ የሚያስችል ጥብቅ የልማት ፕሮጀክት አፈፃጸም የክትትልና ቁጥጥር ሥራን የመወጣት የህዝብ አደራ እንደተሰጠው ገልጸዋል። መንግሥት በፖሊሲ እርምጃና ውጤታማነት፤ ዜጎች ደግሞ በተባባሪነት ጠንካራ የትብብር ቁርኝት በመገንባት የኢትዮጵያን ዕድገት ማፋጠን እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። ዜጎች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገርን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የዴሞክራሲ ባህል ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዳስመሰከሩ ተናግረዋል። በምክር ቤቱ የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ኢሳ ቦሩ፤ በምርጫ ማግስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ፉክክርን ወደ ትብብር በማላቅ ለጠንካራ ዴሞክራሲና ሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ህብረተሰቡ መንግሥትን የማፅናት፤መንግስትም ለህዝብ የገባውን ቃል በመፈጸም ውጤታማ የዕድገት አቅም የሆኑ የልማት ሥራዎችን መገንባት እንዳለበት ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ብልፅግናና ዕድገት ለማረጋገጥና ሀገራዊ የልማት ግቦችን ለማሳካት ሁሉም የበኩሉን ሚና ሊወጣ እንደሚገባም ገልጸዋል። የልማት ግቦችን ለማሳካትና ኢትዮጵያን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ምክር ቤቱ የልማት ግቦችን ከግብ ሊያደርሱ የሚችሉ ሕጎችን የማውጣት ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ስራዎች በስኬት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ህብረተሰቡ ባለው ዕውቀት፣ጉልበትና አቅም ከመንግሥት ጎን በመሰለፍ የኢትዮጵያን እድገት ለማፋጠን የበኩሉን ድርሻ መወጣት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከወርቅ ንግድ ወደ ትግራይ ወጣቶች ሽያጭ ተሸጋግሯል - የወለዶ ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጉዕሽ ግደይ
Jun 29, 2026 1535
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከወርቅ ንግድ ወደ ትግራይ ወጣቶች ሽያጭ መሸጋገሩን የወለዶ ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጉዕሽ ግደይ ገለጹ። የወለዶ ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጉዕሽ ግደይ በወቅታዊ የትግራይ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በዚህም የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በማፍረስና ከውጭ ጠላቶች ጋር በመተባበር ጦርነት ለመጫር በትግራይ ክልል ሁሉንም ፖለቲካዊና ሰላማዊ መንገዶች ዘግቶ በጉልበት የሚያስተዳድርበትን ሁኔታ ፈጥሮ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ለትግራይ ህዝብ ሰላም የፈጠረ ታሪካዊ ስምምነት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሁን እንጂ ያለ ጦርነትና ሁከት መኖር የማይችለው የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ግን ስምምነቱን በተግባር ማፍረሱን ጠቁመዋል። የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም እየተከታተለውና እያወገዘው እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ለዚህም የአውሮፓ ህብረትና የአሜሪካ መንግስት ያወጧቸውን መግለጫዎች በማሳያነት አንስተዋል። የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በመተባበር "ፅምዶ" በሚል ስያሜ እያደረገ ያለው ህገወጥ እንቅስቃሴ የሀገር ክህደት፣ ከህገ-መንግስቱና ከትግራይ ህዝብ ጥቅም አኳያ በተጻራሪ የቆመ ነው ብለዋል። ቡድኑ ሲፈጠር ጀምሮ ለኢትዮጵያ ብሎም ለትግራይ ህዝብ ጥቅም ከመታገል ይልቅ ለኤርትራ መንግስት ጥቅም የታገለበት እንደሚበልጥም አስረድተዋል። የትግራይ ህዝብ ቡድኑ በመራቸው ጦርነቶች ሁሉ ምንም ዓይነት ጥቅም እንዳላገኘ የተናገሩት አቶ ጉዕሽ፤ ይህ የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን አሁንም በተደጋጋሚ በወደቀበት መንገድ እየተጓዘ ከውጭና ከውስጥ ጠላቶች ጋር ተሰልፎ ለጦርነት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቡድኑ የትግራይ ወጣቶችን እያገተና ወላጆችንም እያሰረ ትውልድን ለማጥፋት እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው፤ ይህም መላው የትግራይ ህዝብ ከቡድኑ ጋር እንዳልሆነና በፈቃደኝነት እንደማይዋጋ ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከዚህ ቀደም ወርቅ ይሸጥ እንደነበር ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት ደግሞ የትግራይ ወጣቶችን በመሸጥ የገቢ ምንጩ እያደረጋቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ ከገባበት ቀውስ ለመታደግ ከፌዴራል መንግስት ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አቶ ጉዕሽ፤ ይህ ቡድን እንዲወገድ፣ የትግራይ ህዝብ ዘላቂ ሰላም እንዲያገኝና በቡድኑ ምክንያት ከጎረቤቶችና ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር የተፈጠረውን ቅሬታ ለመፍታት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። የትግራይ ህዝብም ከኢትዮጵያ መንግስትና ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጎን በመሆን ኋላቀሩን የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል። የፌዴራል መንግስትም የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን እስካሁን ለፈጸማቸው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች በትዕግስት፣ በተረጋጋና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑንም ገልፀዋል። ይሁን እንጂ ቡድኑ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ወደ አደገኛ ደረጃ ስለተሸጋገረ የትግራይን ህዝብ ማዳንና የሀገርን ሉዓላዊነት ማስከበር የሚያስችሉ ህገ-መንግስታዊና ፖለቲካዊ ስራዎችን መስራት አለበት ብለዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላም ለማደፍረስ እና ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሱ በሚገኙ የህወሓት ጽንፈኛ አመራር አባላት እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን ይታወሳል።
የኢትዮጵያ እና ቻይና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በትኩረት እየተሰራ ነው
Jun 29, 2026 1314
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ እና ቻይና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ገለጹ፡፡ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የቻይና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ቼን ሀይን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ አምባሳደሩ በዚሁ ወቅት የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት በመጠናቀቁና ብልፅግና ፓርቲ በማሸነፉ ያስተላለፈውን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አድርሰዋል፡፡   ፓርቲው በመልዕክቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት በኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው ሰላምና መረጋጋት፣ ብሔራዊ አንድነትና ሁለንተናዊ ብልጽግና እየተረጋጋጠ እንደሚሄድ ያለውን እምነት ገልጿል፡፡ የምርጫው ውጤት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለብልፅግና ፓርቲ ያለውን ድጋፍ የሚያሳይና በቀጣይም ፓርቲው የኢትዮጵያን ሕዝቦች አስተባብሮ በመምራት ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር የማሻገር ግብን እውን እንደሚያደርግ ጠቅሷል፡፡ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ከዚህ ቀደም የተደረሱ ስምምነቶች ተግባራዊ እንዲደረጉ መስራቱን እንደሚቀጥልና ለሁለቱ ሀገራት እድገት በየትኛውም ሁኔታ የማይናወጥ አጋርነትን እየገነባ እንደሚሄድ አረጋግጧል፡፡ አቶ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ብልፅግና ፓርቲ በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለው የመንግስታትና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲሁም ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ጋር ያለው ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡   ሁለቱ ፓርቲዎች ሀገር በቀል በሆኑ እሳቤዎች እየተመሩ መፍትሄዎችን በማፍለቅ ውጤት ማስመዝገብ መቻላቸውን ገልጸው፤ ዘርፈ ብዙ በሆኑ ጉዳዮች ተባብሮ ከመስራት ባሻገር በተለያየ መስክ እየተደረገ ላለው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ያላቸውን ምስጋና አቅርበዋል፡፡ አምባሳደር ቼን ሀይ በበኩላቸው በብልፅግና ፓርቲ መሪነት በመደመር እሳቤ በኢትዮጵያ እየተመዘገቡ ላሉ ድሎች ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡ በርካታ የቻይና ባለሃብቶች በተለይም በማዕድን፣ በአገልግሎት፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በኮንስትራክሽን በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እያፈሰሱ እንደሚገኙ ነው የገለጹት፡፡ ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ በሁሉም መስኮች የተገኙ ድሎችን ለማስቀጠልና በጋራ ለመስራት በፓርቲዎቹ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ተስማምተዋል፡፡
ጠቅላላ ምርጫው በኢትዮጵያ የሰለጠነ የዴሞክራሲ ሥርዓት ልምምድ እየጎለበተ መምጣቱን ያረጋገጠ ነው-ምሁራን
Jun 29, 2026 973
ሀዋሳ፤ ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፡- በሀገሪቱ የሰለጠነ የፖለቲካ ሥርአት ከመገንባትና ዴሞክራሲን ከማጎልበት አንጻር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የራሱን አሻራ አሳርፏል ሲሉ ምሁራን ገለጹ። በኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት ከተካሄዱ ምርጫዎች በመራጮች ቁጥርም ሆነ በፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ እንዲሁም በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፍትሀዊ ምርጫን በማካሄድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተጠቃሽ ነው። ይህም የምርጫውን ቅቡልነት በማሳደግ ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለሰለጠነ ፖለቲካ ግንባታ ድርሻው የጎላ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገልጸዋል። በጉዳዩ ላይ ሀሳባቸውን የሰጡ ምሁራን እንዳሉት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የሰለጠነ የፖለቲካ ሥርአት ከመገንባት አንጻር የራሱን አሻራ ከማሳረፍ ባለፈ የዴሞክራሲ ልምምድ እየጎለበተ መምጣቱን ያረጋገጠ ነው። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነዜጋና ስነምግባር መምህር ብሩክ ደስታ እንዳሉት ምርጫ ህዝቡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመረጠው መንግስት ብቻ ለመመራት ያለውን ፍላጎት በግልጽ ያሳየበት ወሳኝ ሀገራዊ ሁነት ነው። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ዜጎች ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ዕድገት የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ መሰረት መጣሉንም ጠቅሰዋል። በምርጫው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነ ምግባሩን አክብረው መንቀሳቀስና ህዝቡም በነቂስ ወጥቶ ድምጹን መስጠቱ ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ የድርሻውን ለመወጣት ያለውን ጠንካራ ፍላጎት ያሳያል ብለዋል። እንደ መምህር ብሩክ ገለጻ የመገናኛ ብዙሀንና የሲቪክ ማህበራት በምርጫው ቅድመና ድህረ ሂደት የነበራቸው ተሳትፎ በመንግስት ጠንካራ ተቋማትን ለመገንባት የተሄደበት ርቀትን የሚያሳይ ነው። ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጎልበት የዴሞክራሲ ተቋማት መጠናከር ቁልፍ ድርሻ እንዳለው ገልጸው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መላውን ዜጋ ለማሳተፍ ቴክኖጂን ከመጠቀም ጀምሮ ያደረገው ዝግጅትና የመምራት አቅም የሚደነቅ ነው ብለዋል። ህዝቡም በምርጫው በነቂስ ወጥቶ መሳተፉ ለዴሞክራሲ ሥርአት መጠናከር ካለው ፋይዳ ባለፈ በመረጠው መንግስት ብቻ እንዲተዳደርና በሀገሩም ላይ ተስፋውን እንዲያሳደግ ያደርጋል ሲሉም አክለዋል። የምርጫው ዴሞክራሲያዊነት የመጠላለፍ ፖለቲካ እየቀረና የሀገር ፍላጎት የገባው ትውልድ እየተፈጠረ ስለመምጣቱ አመላካች ነው ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊና ስነሰብ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) ናቸው። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብ ፍላጎትና ውሳኔ የተከበረበትና የኢትዮጵያን ሰላም የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ አካላትን ያሳፈረ መሆኑን ጠቁመዋል። በጠቅላላ ምርጫው አሸናፊ የሆነውና በቀጣይ አዲስ መንግስት የሚመሰርተው ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ የህዝብ አደራ አለበት ያሉት መምህርና ተመራማሪው፣ በተለይ ህዝብ በተለያየ መስክ ላነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በርብርብ መስራት አለበት ብለዋል።          
ሕዝቡ በምርጫው የሰጠን ድምፅ የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፈጥንና የከተማዋን ዕድገት ለማስቀጠል ተጨማሪ ጉልበት የሚፈጥር ነው -ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 29, 2026 1194
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ):-ሕዝቡ በምርጫው የሰጠን ድምፅ የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፈጥንና የከተማዋን ዕድገት ለማስቀጠል ተጨማሪ ጉልበት የሚፈጥር ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ለከተማዋ ነዋሪዎች የምስጋና መርሐ-ግብር አካሂዷል።   በዚሁ የምስጋና መድረክ ላይ የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ በመዲናዋ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ ነዋሪዎቹ ያሳዩት የላቀ ፅናትና ቁርጠኝነት የሚያኮራ እና የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጸዋል። ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ እስከ ድምጽ መስጠት ሂደት ድረስ ነዋሪዎች ያሳዩት አስደናቂ የዴሞክራሲ ተሳትፎ ታሪካዊ እንደነበርም ነው የጠቆሙት።   በምርጫው ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው ውጤት በከተማዋ የተጀመረውን የልማትና የብልፅግና ጉዞ ይበልጥ ለማስቀጠል ተጨማሪ ጉልበት እና መነቃቃት የሚሰጥ መሆኑን አስገንዝበዋል። የከተማ አስተዳደሩ ሌት ተቀን በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል፣ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ውብና ሳቢ የማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ፖለቲካ
ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ጉልህ ድርሻ ያበረክታሉ
Jun 30, 2026 22
ሐረር፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምክክሩ የተለዩት አጀንዳዎች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት ያላቸው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን በሐረር የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረጋቸው ተከታታይ ውይይቶች፤ ለዘመናት የቆዩ መዋቅራዊ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ለይቶ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ይህንኑ አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሐረር ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች፤ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው የተለዩት አጀንዳዎች ወቅታዊና ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሐረሪ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች ጥምረት ሰብሳቢ አቶ መሐመድ ዩሱፍ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ከጥምረቱ ጋር በቅንጅት እየሠራ ሲሆን፣ እስካሁን ባለው ሂደትም አበረታች ተግባራትን አከናውኗል። ኮሚሽኑ የለያቸው አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ለመገንባትና ለዘመናት ሳያግባቡ የቆዩ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሀገር ሽማግሌው አቶ መሀመድ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ያሉ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የሀገራዊ ምክክሩ ሚና ከፍተኛ ነው። በመሆኑም ለዚህ ሂደት ስኬታማነት ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽኦ ማበርከት ይገባናል ብለዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የማያግባቡ ጉዳዮችን በውይይት ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፤ ጠንካራ ሥርዓተ-መንግስት ለመገንባት፣ የጋራ ትርክትን ለማስረጽና ዴሞክራሲን ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው የገለጹት ደግሞ አባገዳ አህመድ ዩስፍ ናቸው። ኮሚሽኑ ሰሞኑን ይፋ ያደረገው አጀንዳ በሀገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍና ልዩነቶችን ወደ ትብብር በመቀየር ዘላቂ ሰላምን እንደሚያሰፍን ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።   በክልሉ የጀንኤላ ወረዳ የሰላም ቤተሰብ ሰብሳቢ መምህርት ሒሩት ታደሰ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በሀገሪቱ የነበሩ አለመግባባቶችን እስከ ታችኛው የህብረተሰብ ክፍል በመውረድ ለመፍታትና ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት እያከናወነ የሚገኘውን ተግባር አድንቀዋል። ኮሚሽኑ አጀንዳዎችን ለይቶ ወደ ስራ መግባቱ ኢትዮጵያን ወደ አንድነት የሚያመጣ፣ ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍንና ጠንካራ ሀገረ-መንግስት ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህንን ታሪካዊ ዕድል በመጠቀም ሰላማዊና የተሻለች ሀገር ለመገንባት እያበረከቱ የሚገኘውን አስተዋጽኦ ይበልጥ እንደሚያጠናክሩም አክለው ገልጸዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት የሀገርን ዕድገትና ብልፅግና የሚያፋጥኑ ተግባራት ላይ ትኩረት ሊያደርግ ይገባል
Jun 30, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሰረት የሚመሰረተው አዲስ መንግሥት የሀገርን ዕድገትና ብልፅግና ለሚያፋጥኑ የልማት ስራዎች ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ምሁራን ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ብልፅግና ፓርቲ መንግሥት ለመመስረት የሚያስችለውን አብላጫ ድምፅ አግኝቷል፡፡ በመሆኑም አሸናፊው ብልፅግና ፓርቲ በመጪው መስከረም ወር ላይ አዲስ መንግሥት የሚመሰርት ይሆናል፡፡ አዲስ የሚመሰረተውን መንግሥት በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን፥ አዲሱ መንግሥት ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ፣ አብሮነትና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር ላይ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል ብለዋል። ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የሀገር ዕድገትና ብልፅግናን የሚያፋጥኑ ተግባራትን በስኬት ማከናወን እንዳለበትም ነው ያነሱት። በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የስነ መንግሥትና ሕዝብ አስተዳደር ተመራማሪና ተንታኝ ጫሊ ኢተፋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ምርጫ ሕዝብ ድምፅ ለሰጠው ፓርቲ አደራና ኃላፊነት የሚያስረክብበት የዴሞክራሲ ሂደት ነው። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መካሄዱን ጠቅሰው፥ በምርጫው ውጤት መሰረት አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት የተጀመሩ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳሩን የማስፋት ስራዎች ማስቀጠል አለበት ብለዋል። የትኛውም ሀገራዊ ችግር በምክክርና በውይይት ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኝ በሆደ ሰፊነት መሥራት እንዳለበትም ጠቁመዋል። በተጨማሪም ለመልካም አስተዳደርና ለሀገር እድገት ማነቆ የሆኑ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን የሚያስቀሩ ፖሊሲዎችና አሰራሮችን በተደራጀ መልኩ መተግበር ይጠበቅበታል ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት በሚል መርህ እየተከተለች ያለው ቀጣናዊ ትስስርን የማጠናከር የመሪነት ሚናዋን ማስቀጠልም አለበት ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰላምና ደህንነት መምህርና ተመራማሪ ሙሉጌታ አየለ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በቀጣይ የሚመሰረተው መንግሥት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ዘርፉን ይበልጥ በማዘመን ብልሹ አሠራርን ማስቀረት ቀዳሚ የቤት ሥራው ሊሆን እንደሚገባ አንስተዋል። ለዚህም የተጀመረው የጠንካራ ተቋማት ግንባታ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ነው የተናገሩት። የሥራ ዕድል የሚፈጥሩና የሉዓላዊነት ቁልፍ አጀንዳ የሆነውን በምግብ ራስን የመቻል ግብን የሚያረጋግጡ የፖሊሲ ትግበራዎችን ማጠናከር ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ ሥራዎች ናቸው ብለዋል።
አዲስ የሚዋቀረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገራዊ ለውጡ የፈጠረውን የብልፅግና ጉዞ የማስቀጠል የህዝብ አደራ አለበት
Jun 30, 2026 166
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሰረት የሚዋቀረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ የፈጠረውን የብልፅግና ጉዞ የማስቀጠል የህዝብ አደራ እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሁሉን አቀፍ፣ ነፃ፣ ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ በሆነና ድምፅ በሚስጥር በሚሰጥበት ሥርዓት በየአምስት ዓመቱ በሕዝብ እንደሚመረጡ በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥቱ አንቀፅ-54 ላይ በግልፅ ተመላክቷል። የምክር ቤቱ አባላትም የመላው ሕዝብ ተወካዮች በመሆናቸው ተገዥነታቸው ለሕገ-መንግሥቱ፣ ለሕዝቡና ለሕሊናቸው ብቻ መሆኑን በሕዝብ ውክልና የክትትልና ቁጥጥር ኃላፊነት እንደተሰጣቸው ተቀምጧል። በሕገ-መንግሥት አንቀፅ-58 መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚመረጠው ለአምስት ዓመታት ነው፤ የሥራ ዘመኑም ከማብቃቱ አንድ ወር በፊት አዲስ ምርጫ ተካሂዶ ይጠናቀቃል። ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎም በመጪው መስከረም ወር አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ አዲስ መንግሥት እንደሚመሰርት ይጠበቃል። ስድስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመንም በዚህ ዓመት የሚጠናቀቅ ሲሆን፤ በመጪው መስከረም አዲሱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚቋቋም ይሆናል። በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጀ እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎችን የልማት፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ጽኑ ፍላጎት አስመስክሯል። ሕብረተሰቡ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ጭምር በመሰለፍ ይወክለኛል ለሚለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ መስጠቱም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየቱን ገልጸዋል። በጠቅላላ ምርጫው ውጤት መሰረት የሚዋቀረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ የፈጠረውን የብልፅግና ጉዞ የማስቀጠል የህዝብ አደራ እንዳለበት ተናግረዋል። በቀጣይ መስከረም በይፋ ሥራውን የሚጀምረው አዲሱ ምክር ቤትም የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች የሚያፋጥን ጥብቅ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ እንደሚጠበቅበት አንስተዋል። በተለይም ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች በስኬት ተጠናቀው የሀገርና ህዝብ ሁለንተናዊ የዕድገት አቅም እንዲሆኑ የማድረግ ታሪካዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደሚጠይቅ አስረድተዋል። በምክር ቤቱ የጤና፣ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ በርካታ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ነው ብለዋል። አዲሱ ምክር ቤትም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ የሚያስችል ጥብቅ የልማት ፕሮጀክት አፈፃጸም የክትትልና ቁጥጥር ሥራን የመወጣት የህዝብ አደራ እንደተሰጠው ገልጸዋል። መንግሥት በፖሊሲ እርምጃና ውጤታማነት፤ ዜጎች ደግሞ በተባባሪነት ጠንካራ የትብብር ቁርኝት በመገንባት የኢትዮጵያን ዕድገት ማፋጠን እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። ዜጎች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገርን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የዴሞክራሲ ባህል ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዳስመሰከሩ ተናግረዋል። በምክር ቤቱ የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ኢሳ ቦሩ፤ በምርጫ ማግስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ፉክክርን ወደ ትብብር በማላቅ ለጠንካራ ዴሞክራሲና ሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ህብረተሰቡ መንግሥትን የማፅናት፤መንግስትም ለህዝብ የገባውን ቃል በመፈጸም ውጤታማ የዕድገት አቅም የሆኑ የልማት ሥራዎችን መገንባት እንዳለበት ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ብልፅግናና ዕድገት ለማረጋገጥና ሀገራዊ የልማት ግቦችን ለማሳካት ሁሉም የበኩሉን ሚና ሊወጣ እንደሚገባም ገልጸዋል። የልማት ግቦችን ለማሳካትና ኢትዮጵያን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ምክር ቤቱ የልማት ግቦችን ከግብ ሊያደርሱ የሚችሉ ሕጎችን የማውጣት ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ስራዎች በስኬት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ህብረተሰቡ ባለው ዕውቀት፣ጉልበትና አቅም ከመንግሥት ጎን በመሰለፍ የኢትዮጵያን እድገት ለማፋጠን የበኩሉን ድርሻ መወጣት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከወርቅ ንግድ ወደ ትግራይ ወጣቶች ሽያጭ ተሸጋግሯል - የወለዶ ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጉዕሽ ግደይ
Jun 29, 2026 1535
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከወርቅ ንግድ ወደ ትግራይ ወጣቶች ሽያጭ መሸጋገሩን የወለዶ ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጉዕሽ ግደይ ገለጹ። የወለዶ ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጉዕሽ ግደይ በወቅታዊ የትግራይ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በዚህም የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በማፍረስና ከውጭ ጠላቶች ጋር በመተባበር ጦርነት ለመጫር በትግራይ ክልል ሁሉንም ፖለቲካዊና ሰላማዊ መንገዶች ዘግቶ በጉልበት የሚያስተዳድርበትን ሁኔታ ፈጥሮ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ለትግራይ ህዝብ ሰላም የፈጠረ ታሪካዊ ስምምነት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሁን እንጂ ያለ ጦርነትና ሁከት መኖር የማይችለው የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ግን ስምምነቱን በተግባር ማፍረሱን ጠቁመዋል። የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም እየተከታተለውና እያወገዘው እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ለዚህም የአውሮፓ ህብረትና የአሜሪካ መንግስት ያወጧቸውን መግለጫዎች በማሳያነት አንስተዋል። የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በመተባበር "ፅምዶ" በሚል ስያሜ እያደረገ ያለው ህገወጥ እንቅስቃሴ የሀገር ክህደት፣ ከህገ-መንግስቱና ከትግራይ ህዝብ ጥቅም አኳያ በተጻራሪ የቆመ ነው ብለዋል። ቡድኑ ሲፈጠር ጀምሮ ለኢትዮጵያ ብሎም ለትግራይ ህዝብ ጥቅም ከመታገል ይልቅ ለኤርትራ መንግስት ጥቅም የታገለበት እንደሚበልጥም አስረድተዋል። የትግራይ ህዝብ ቡድኑ በመራቸው ጦርነቶች ሁሉ ምንም ዓይነት ጥቅም እንዳላገኘ የተናገሩት አቶ ጉዕሽ፤ ይህ የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን አሁንም በተደጋጋሚ በወደቀበት መንገድ እየተጓዘ ከውጭና ከውስጥ ጠላቶች ጋር ተሰልፎ ለጦርነት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቡድኑ የትግራይ ወጣቶችን እያገተና ወላጆችንም እያሰረ ትውልድን ለማጥፋት እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው፤ ይህም መላው የትግራይ ህዝብ ከቡድኑ ጋር እንዳልሆነና በፈቃደኝነት እንደማይዋጋ ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን ከዚህ ቀደም ወርቅ ይሸጥ እንደነበር ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት ደግሞ የትግራይ ወጣቶችን በመሸጥ የገቢ ምንጩ እያደረጋቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ ከገባበት ቀውስ ለመታደግ ከፌዴራል መንግስት ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አቶ ጉዕሽ፤ ይህ ቡድን እንዲወገድ፣ የትግራይ ህዝብ ዘላቂ ሰላም እንዲያገኝና በቡድኑ ምክንያት ከጎረቤቶችና ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር የተፈጠረውን ቅሬታ ለመፍታት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። የትግራይ ህዝብም ከኢትዮጵያ መንግስትና ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጎን በመሆን ኋላቀሩን የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል። የፌዴራል መንግስትም የሕወሃት ፅንፈኛ ቡድን እስካሁን ለፈጸማቸው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች በትዕግስት፣ በተረጋጋና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑንም ገልፀዋል። ይሁን እንጂ ቡድኑ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ወደ አደገኛ ደረጃ ስለተሸጋገረ የትግራይን ህዝብ ማዳንና የሀገርን ሉዓላዊነት ማስከበር የሚያስችሉ ህገ-መንግስታዊና ፖለቲካዊ ስራዎችን መስራት አለበት ብለዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ ሰላም ለማደፍረስ እና ግጭት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሱ በሚገኙ የህወሓት ጽንፈኛ አመራር አባላት እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏን ይታወሳል።
የኢትዮጵያ እና ቻይና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በትኩረት እየተሰራ ነው
Jun 29, 2026 1314
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ እና ቻይና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ገለጹ፡፡ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የቻይና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ቼን ሀይን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ አምባሳደሩ በዚሁ ወቅት የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት በመጠናቀቁና ብልፅግና ፓርቲ በማሸነፉ ያስተላለፈውን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አድርሰዋል፡፡   ፓርቲው በመልዕክቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት በኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው ሰላምና መረጋጋት፣ ብሔራዊ አንድነትና ሁለንተናዊ ብልጽግና እየተረጋጋጠ እንደሚሄድ ያለውን እምነት ገልጿል፡፡ የምርጫው ውጤት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለብልፅግና ፓርቲ ያለውን ድጋፍ የሚያሳይና በቀጣይም ፓርቲው የኢትዮጵያን ሕዝቦች አስተባብሮ በመምራት ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር የማሻገር ግብን እውን እንደሚያደርግ ጠቅሷል፡፡ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ከዚህ ቀደም የተደረሱ ስምምነቶች ተግባራዊ እንዲደረጉ መስራቱን እንደሚቀጥልና ለሁለቱ ሀገራት እድገት በየትኛውም ሁኔታ የማይናወጥ አጋርነትን እየገነባ እንደሚሄድ አረጋግጧል፡፡ አቶ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ብልፅግና ፓርቲ በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለው የመንግስታትና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲሁም ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ጋር ያለው ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡   ሁለቱ ፓርቲዎች ሀገር በቀል በሆኑ እሳቤዎች እየተመሩ መፍትሄዎችን በማፍለቅ ውጤት ማስመዝገብ መቻላቸውን ገልጸው፤ ዘርፈ ብዙ በሆኑ ጉዳዮች ተባብሮ ከመስራት ባሻገር በተለያየ መስክ እየተደረገ ላለው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ያላቸውን ምስጋና አቅርበዋል፡፡ አምባሳደር ቼን ሀይ በበኩላቸው በብልፅግና ፓርቲ መሪነት በመደመር እሳቤ በኢትዮጵያ እየተመዘገቡ ላሉ ድሎች ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡ በርካታ የቻይና ባለሃብቶች በተለይም በማዕድን፣ በአገልግሎት፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በኮንስትራክሽን በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እያፈሰሱ እንደሚገኙ ነው የገለጹት፡፡ ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ በሁሉም መስኮች የተገኙ ድሎችን ለማስቀጠልና በጋራ ለመስራት በፓርቲዎቹ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ተስማምተዋል፡፡
ጠቅላላ ምርጫው በኢትዮጵያ የሰለጠነ የዴሞክራሲ ሥርዓት ልምምድ እየጎለበተ መምጣቱን ያረጋገጠ ነው-ምሁራን
Jun 29, 2026 973
ሀዋሳ፤ ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፡- በሀገሪቱ የሰለጠነ የፖለቲካ ሥርአት ከመገንባትና ዴሞክራሲን ከማጎልበት አንጻር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የራሱን አሻራ አሳርፏል ሲሉ ምሁራን ገለጹ። በኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት ከተካሄዱ ምርጫዎች በመራጮች ቁጥርም ሆነ በፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ እንዲሁም በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፍትሀዊ ምርጫን በማካሄድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተጠቃሽ ነው። ይህም የምርጫውን ቅቡልነት በማሳደግ ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለሰለጠነ ፖለቲካ ግንባታ ድርሻው የጎላ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገልጸዋል። በጉዳዩ ላይ ሀሳባቸውን የሰጡ ምሁራን እንዳሉት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የሰለጠነ የፖለቲካ ሥርአት ከመገንባት አንጻር የራሱን አሻራ ከማሳረፍ ባለፈ የዴሞክራሲ ልምምድ እየጎለበተ መምጣቱን ያረጋገጠ ነው። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነዜጋና ስነምግባር መምህር ብሩክ ደስታ እንዳሉት ምርጫ ህዝቡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመረጠው መንግስት ብቻ ለመመራት ያለውን ፍላጎት በግልጽ ያሳየበት ወሳኝ ሀገራዊ ሁነት ነው። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ዜጎች ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ዕድገት የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ መሰረት መጣሉንም ጠቅሰዋል። በምርጫው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነ ምግባሩን አክብረው መንቀሳቀስና ህዝቡም በነቂስ ወጥቶ ድምጹን መስጠቱ ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ የድርሻውን ለመወጣት ያለውን ጠንካራ ፍላጎት ያሳያል ብለዋል። እንደ መምህር ብሩክ ገለጻ የመገናኛ ብዙሀንና የሲቪክ ማህበራት በምርጫው ቅድመና ድህረ ሂደት የነበራቸው ተሳትፎ በመንግስት ጠንካራ ተቋማትን ለመገንባት የተሄደበት ርቀትን የሚያሳይ ነው። ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጎልበት የዴሞክራሲ ተቋማት መጠናከር ቁልፍ ድርሻ እንዳለው ገልጸው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መላውን ዜጋ ለማሳተፍ ቴክኖጂን ከመጠቀም ጀምሮ ያደረገው ዝግጅትና የመምራት አቅም የሚደነቅ ነው ብለዋል። ህዝቡም በምርጫው በነቂስ ወጥቶ መሳተፉ ለዴሞክራሲ ሥርአት መጠናከር ካለው ፋይዳ ባለፈ በመረጠው መንግስት ብቻ እንዲተዳደርና በሀገሩም ላይ ተስፋውን እንዲያሳደግ ያደርጋል ሲሉም አክለዋል። የምርጫው ዴሞክራሲያዊነት የመጠላለፍ ፖለቲካ እየቀረና የሀገር ፍላጎት የገባው ትውልድ እየተፈጠረ ስለመምጣቱ አመላካች ነው ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊና ስነሰብ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) ናቸው። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብ ፍላጎትና ውሳኔ የተከበረበትና የኢትዮጵያን ሰላም የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ አካላትን ያሳፈረ መሆኑን ጠቁመዋል። በጠቅላላ ምርጫው አሸናፊ የሆነውና በቀጣይ አዲስ መንግስት የሚመሰርተው ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ የህዝብ አደራ አለበት ያሉት መምህርና ተመራማሪው፣ በተለይ ህዝብ በተለያየ መስክ ላነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በርብርብ መስራት አለበት ብለዋል።          
ሕዝቡ በምርጫው የሰጠን ድምፅ የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፈጥንና የከተማዋን ዕድገት ለማስቀጠል ተጨማሪ ጉልበት የሚፈጥር ነው -ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 29, 2026 1194
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ):-ሕዝቡ በምርጫው የሰጠን ድምፅ የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፈጥንና የከተማዋን ዕድገት ለማስቀጠል ተጨማሪ ጉልበት የሚፈጥር ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ለከተማዋ ነዋሪዎች የምስጋና መርሐ-ግብር አካሂዷል።   በዚሁ የምስጋና መድረክ ላይ የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ በመዲናዋ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ ነዋሪዎቹ ያሳዩት የላቀ ፅናትና ቁርጠኝነት የሚያኮራ እና የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጸዋል። ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ እስከ ድምጽ መስጠት ሂደት ድረስ ነዋሪዎች ያሳዩት አስደናቂ የዴሞክራሲ ተሳትፎ ታሪካዊ እንደነበርም ነው የጠቆሙት።   በምርጫው ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው ውጤት በከተማዋ የተጀመረውን የልማትና የብልፅግና ጉዞ ይበልጥ ለማስቀጠል ተጨማሪ ጉልበት እና መነቃቃት የሚሰጥ መሆኑን አስገንዝበዋል። የከተማ አስተዳደሩ ሌት ተቀን በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል፣ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ውብና ሳቢ የማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ
በከተማዋ ተገንብቶ ወደ ስራ የገባው መናኸሪያ የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር አስችሏል
Jun 30, 2026 33
ሚዛን አማን፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሚዛን አማን ከተማ ተገንብቶ ወደ ስራ የገባው አዲሱ መናኸሪያ የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር ምቹ ሁኔታን መፍጠሩን አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎች ገለጹ። በቅርቡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሚዛን አማን ከተማ የተገነባው አዲስ መናኸሪያ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ይታወሳል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የመናኸሪያው ተገልጋዮች እንደገለፁት፤ አዲሱ መናኸሪያ ከዚህ ቀደም የነበረውን የመጥበብና የንጽህና ጉድለት ችግር በማስቀረት የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር አስችሏል። ይህም መንግስት ሕዝብን ለእንግልት ይዳርጉ የነበሩ የመሠረተ ልማት ክፍተቶችን ለይቶ በማዘመን ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ መሆኑን የሚያመላክት እንደሆነም ተናግረዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል በዛብህ በቀለ እና አብዮት ወልደማርያም፤ ከዚህ ቀደም የነበረው መናኸሪያ ጠባብ በመሆኑ ቶሎ ስለሚሞላ አገልግሎት የሚሰጡበትን ተሽከርካሪ ውጭ ለማሳደር ይገደዱ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህም ለተሽከርካሪዎች ደህንነት ምቹ እንዳልነበር በማንሳት የእቃ መጥፋትና ለፓርኪንግ ወጪ የማውጣት ጫና ፈጥሮብን ቆይቷል አሁን ግን ይህ ችግር ተቀርፎልናል ብለዋል። አዲሱ መናኸሪያ በአግባቡ ተጠብቆ እንዲዘልቅ የበኩላችንን ኃላፊነት እንወጣለን ብለዋል።   ከተሳፋሪዎች መካከል ወይዘሮ ዓለሚቱ ገረመው እና ታደለ ኃይለኢየሱስ፤ አዲሱ መናኸሪያ የተሻለ በመሆኑ ደህንነታቸው ተጠብቆ በሥነ ሥርዓት አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል። ቀደም ሲል በዝናብ ጊዜ በሚፈጠረው ጭቃ ምክንያት ለመውጣትና መግባት እንኳ ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰው መንግስት ደረጃውን የጠበቀ ግንባታ በማከናወን ለችግሩ መፍትሔ በመስጠቱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘመዴ አንዳርጌ፤ በክልሉ የሚታዩ የመናኸሪያ አገልግሎት ችግሮችን ለመቅረፍ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።   ከ425 በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግደው የሚዛን አማን መናኸሪያ በውስጡ የትራንስፖርት ማኅበራት ቢሮ፣ የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት፤ ካፍቴሪያና ሌሎች ክፍሎችንም ያሟላ ነው ብለዋል። ለግንባታው ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸው ለተሳፋሪዎች ምቹ ማረፊያና ሰፊ መንቀሳቀሻ እንዲኖረው ተደርጎ መሰራቱን ጠቁመዋል። በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ መናኸሪያዎች በዲጂታል ሲስተም ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን በቅርቡ የተመረቀውን የታርጫና በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የቦንጋ መናኸሪያዎች ለአብነት ጠቅሰዋል።
መገናኛ ብዙሃን ለስርዓተ ጾታ እኩልነት ይበልጥ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል
Jun 30, 2026 110
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ለስርዓተ ጾታ እኩልነት ይበልጥ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ ገለጹ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ከኢንተርናሽናል ሚዲያ ስፖርት (IMS) ጋር በመተባበር፤ በስርዓተ ጾታ እና የሴት ጋዜጠኞችን ማብቃት ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት እያካሄደ ይገኛል።   በዚህ መድረክ ላይ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ድርጅቶች የተወጣጡ ሴት ጋዜጠኞች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው። ዋና ዳይሬክተሯ ሃይማኖት በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ መገናኛ ብዙኃን የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማስፈን ለሚከናወኑ ተግባራት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል። በተለይም ሴቶች በህብረተሰቡ ውስጥ ያላቸውን ጉልህ ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት፣ በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ በአመራርነትና በውሳኔ ሰጪነት ደረጃ ሊጎለብት እንደሚገባ አሳስበዋል። የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 ሴቶች የሕብረተሰቡ ግማሽ አካል እንደመሆናቸው መጠን እንደ የዕድሜያቸውና እንደ የስርዓተ-ፆታ ፍላጎታቸዉ፣ ተግዳሮቶቻቸውንና እምቅ አቅማቸዉን የሚመጥኑ ፕሮግራሞች ሊዘጋጁላቸው እንደሚገባ ይደነግጋል ብለዋል። ሴቶች በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ንቁ ተጠቃሚና ውሳኔ ሰጪ እንዲሆኑ የሚያስገድዱ ጠንካራ መርሆዎች መኖር እንዳለባቸውም በአዋጁ መደንገጉን ጠቅሰዋል፡፡ በማንኛውም የመገናኛ ብዙኃን ውጤት ሴቶችን ዝቅ አድርጎ የማቅረብ አዝማሚያ በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፤ የሴቶችን ክብርና እኩልነት የመጠበቅ የሕግ ግዴታም መጣሉን ነው የገለጹት፡፡ በተጨማሪም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ ደረጃ የሴቶችን መብት፣ ውክልናና ተሳትፎ ለማጠናከር በርካታ ስምምነቶችን ተቀብላ እየተገበረች መሆኑን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት በብዙ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ውስጥ በአመራር ደረጃ፣ በውሳኔ ሰጪነት እና በይዘት ዝግጅት ሂደት ላይ የሴቶች ተሳትፎ መሻሻሎችን እያሳየ ቢሆንም ይበልጥ ሊጎለብት ይገባል ብለዋል፡፡   ይህንን ለማቃለል በመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ውስጥ ጠንካራ የስርዓተ ጾታ ምላሽ ሰጪ የመገናኛ ብዙኃን ፖሊሲዎችን፣ የሴት ባለሙያዎችን የሥራ አካባቢ ደህንነት የሚያረጋግጡ መመሪያዎችን እና ግልጽ የክትትልና የተጠያቂነት አሰራር መዘርጋት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። በቀጣይም የሴቶችን ተሳትፎና አመራር ሰጪነት ማጠናከር፣ በይዘት ምርትና ስርጭት ሂደት የስርዓተ ጾታ ሚዛንን ማረጋገጥ፣ ከፆታዊ ትንኮሳ ነፃ የሆነ ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር፣ የሚዲያ ይዘቶችን በስርዓተ ጾታ መነፅር መከታተል፣ አግላይና አድሎአዊ የሆኑ ቋንቋዎችን ማስወገድ፣ ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታና ሥልጠና ሥርዓት ማበጀት ይገባል ብለዋል። መገናኛ ብዙኃን የተጠናከረ የስርዓተ ፆታ ኤዲቶሪያል አሰራር በመዘርጋት፣ ለስርዓተ ፆታ ጉዳዮች በቂ የአየር ሰዓትና ሽፋን በመስጠት፣ ሕግና የሙያውን ሥነ-ምግባር አክብረው የሚያቀርቡበትን አሠራር መዘርጋት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ በአጽንኦት አሳስበዋል።
በክልሉ ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ  ፈተና ስኬታማነት ዝግጅት ተደርጓል
Jun 30, 2026 93
ጋምቤላ ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ስኬታማ ለማድረግ አስፈላጊው ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል። የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡኩኝ ኦኬሎ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ስኬታማነት ዝግጅት ሲደረግ ቆይቶ በዛሬው ዕለት የፈተና አሰጣጥ ሂደቱ በስኬት ተጀምሯል።   በክልሉ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን 8 ሺህ 536 የተፈጥሮና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን በበይነመረብና በወረቀት ለማስፈተን ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። ከተፈታኞቹ መካከል 1 ሺህ 448 ተማሪዎች በበይነመረብ (ኦንላይን) በስድስት ዙር እንደሚፈተኑ ጠቁመው፤ በዛሬው ዕለት የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፈተናውን እየወሰዱ መሆናቸውን ተናግረዋል። በበይነመረብ (ኦንላይን) የሚሰጠው ፈተና በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ በጋምቤላ ከተማ ኤልያና ብርሃን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፤ የወረቀት ተፈታኝ ተማሪዎች ደግሞ ፈተናውን የሚወስዱት በጋምቤላና በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲዎች መሆኑን ገልጸዋል።
በኦሮሚያ ክልል የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የሚሰሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jun 30, 2026 172
ሮቤ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ እየተሰሩ የሚገኙ ተግባራት ይበልጥ እንደሚጠናከሩ የኦሮሚያ ክልል ትራንስፖርት ኤጀንሲ አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል ትራንስፖርት ኤጀንሲ ከኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር «የትራፊክ አደጋን በጋራ እንከላከል» በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው የትራፊክ ሳምንት በባሌ ሮቤ ከተማ ተከብሯል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ትራንስፖርት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ከማል ማሜ እንዳሉት፤ በክልሉ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ እየተሰሩ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ።   በተለይም የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ቁጥጥርን በማጠናከርና ግንዛቤን በማሳደግ፣ በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በባሌ ሮቤ የተከበረው የትራፊክ ሳምንት ኅብረተሰቡ በትራፊክ ሕግ እና ደንብ ዙሪያ ያለውን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል በክረምቱ ወራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል የትራፊክ ደህንነትና ግንዛቤ መፍጠር አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል። የፌደራል የመንገድ ደህንነት እና መድህን ፈንድ አገልግሎት ምክትል ኃላፊ አቶ መሐመድ ሐሰን በበኩላቸው፤ የትራንስፖርት ዘርፉ ሀገሪቱ ለተያያዘችው የለውጥ ሂደት ስኬታማነት ከፍተኛ ሚና እንዳለው አስታውሰዋል።   ይሁን እንጂ ለትራፊክ ደህንነት መረጋገጥ የተቀናጀ አሠራር ባለመዘርጋቱ አደጋው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ይህም በዜጎች ላይ የሕይወት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት ከማስከተሉም በላይ፣ በከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በተገነቡ የመንገድ መሠረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ውድመት እያደረሰ ነው ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ35 ሺህ በላይ የትራፊክ አደጋዎች መድረሳቸውንና በአደጋውም የ2 ሺህ 800 ዜጎች ሕይወት ማለፉን የገለጹት አቶ መሐመድ፤ ይህም የችግሩን አሳሳቢነት በግልጽ እንደሚያሳይ ተናግረዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከልም የሕግ ማዕቀፎችንና የተሽከርካሪ ደረጃዎችን ማሻሻል፣ የትራፊክ ቁጥጥር ሂደትን ማዘመን፣ ዘርፉን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደገፍ የተጀመሩና ተጠናክረው የሚቀጥሉ ሥራዎች መሆናቸውን አብራርተዋል። የባሌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም ኃይሌ በበኩላቸው፤ የትራፊክ ሳምንት መከበሩ የኅብረተሰቡን የትራፊክ ግንዛቤ ለማጎልበትና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚረዳ ገልጸዋል።   የሮቤ ከተማ ከንቲባ አቶ ዲኖ አሚን ደግሞ በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ፣ የትራፊክ ፍሰቱን በማሳለጥ አደጋን ለመቀነስ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። በመርሐግብሩ ማጠቃለያ ላይ በትራፊክ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሌሎች ዜጎችን የማሰብ ሥነ ሥርዓት በሻማ ማብራትና የእግር ጉዞ ተከናውኗል። በዝግጅቱ ላይ በከተማዋ የሚገኙ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋማት፣ የባጃጅ ተሽከርካሪ ማኅበራት፣ ነዋሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢኮኖሚ
በቱሪዝም ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት የሀገርን ኢኮኖሚና ገጽታ ለመገንባት የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ
Jun 30, 2026 90
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በቱሪዝም ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት የሀገርን ኢኮኖሚና ገጽታ ለመገንባት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ። የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩት “የላቀ ክህሎት ለቱሪዝም እድገት” በሚል መሪ ቃል 13ኛውን የቱሪዝምና የመስተንግዶ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር ጀምሯል።   በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ፣ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ተዋናዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ መንግሥት በቱሪዝም ዘርፉ ውጤታማና ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። ይህንን ማሻሻያ ተከትሎም የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩትን የማጠናከር ሥራ የተሠራ ሲሆን፣ ተቋሙ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የቱሪዝም መስኮች ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ማፍራት መቻሉን ጠቁመዋል። ኢንስቲትዩቱ ከመደበኛ ትምህርት በተጨማሪ አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት ለበርካታ ዜጎች መድረስ መቻሉን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በዚህም ለብዙዎች የሥራ ዕድል እየተፈጠረ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዘርፉ ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለውጭ ሀገራት ገበያም ተወዳዳሪ መሆን የሚችል የሰው ኃይል እየፈራ ይገኛል፤ ይህ ተግባር ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። ቱሪዝም ካለው ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ባሻገር ለሀገር ገጽታ ግንባታ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው በቀጣይም የአገልግሎት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ በልዩ ትኩረት መሥራት ይገባል ብለዋል። የቱሪዝምና መስተንግዶ ሳምንት መከበሩ፣ የሥራ ገበያውንና የሰለጠነውን የሰው ኃይል በቀጥታ ለማገናኘት እንዲሁም ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዱ ጠቃሚ ግብዓቶችን ለመሰብሰብ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።   የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ በበኩላቸው፤ ተቋሙ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን በማፍራት ለኢንዱስትሪው ዕድገት የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝና በቀጣይም ይህንን ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የዘንድሮው የቱሪዝምና መስተንግዶ ሳምንትም ኢንስቲትዩቱን ይበልጥ ውጤታማ ሊያደርጉ በሚችሉና ዘርፉን በሚያሳድጉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር ገልጸዋል።
የመሬት አካውንት መግለጫና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታ ይፋ ሆነ
Jun 30, 2026 178
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው፣ አካታችና የማይበገር ዕድገት ለማስመዝገብ ለምታደርገው ጥረት ጠቃሚ መሰረት ሆኖ የሚያገለግለው የመሬት አካውንት መግለጫና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታ ይፋ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዕትም የመሬት አካውንት መግለጫ ሪፖርት እና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታን ይፋ የማድረጊያ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል። በዚህ ይፋዊ መድረክ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍስሃፅዮን፣ የዓለም ባንክ የኦፕሬሽን ማናጀር ጁልያን ቪክቶር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍሰሃፅዮን በመድረኩ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፤ ይፋ የሆኑት ሰነዶች ሀገራዊ የጋራ ራዕይን እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም አላቸው። በተለይም በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ለመቅረጽ፣ የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል፣ ቀጣይነት ያለው ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጋራ ለመስራት ያለንን ቁርጠኝነት የምናሳይበት ነው ብለዋል።   እነዚህ ሰነዶች ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት በተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች የተዘጋጁ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህም የላቀ የትብብር ውጤት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። ሰነዶቹ የተዘጋጁት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር በሚመራው ስቲሪንግ ኮሚቴ፣ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ተቋማት የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሆነም አክለዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በአህጉሪቱ ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት የቻለች ብሎም የሚጨበጥ ስኬት ያስመዘገበች ሀገር መሆኗንም ጠቅሰዋል፡፡ ይህ ያስመዘገበችው ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገትም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ህይወት በተጨባጭ መለወጡን ጠቁመዋል። ለዚህ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ስኬት ለመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ለጤና እና ለትምህርት የተሰጠው ከፍተኛ ትኩረትና በሌሎችም የተደረገው ኢንቨስትመንት ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷልም ብለዋል። ቀጣይነት ያለውን ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተፈጥሮ ሀብቶችን የመጠበቅ፣ የመንከባከብና የማልማት ተግባራትም በተሳካ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡
ቡናን በጥራት በማምረት በዓመቱ የታቀደውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ ነው
Jun 30, 2026 167
ሃዋሳ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ቡናን በጥራት በማምረት በዓመቱ የታቀደውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ ኢትዮጵያ ከቡና ገዢ ደንበኞቿ በተጨማሪ ከ20 በላይ አዳዲስ የዓለም ገበያዎችን መቀላቀሏ ይታወቃል። ከኢትዮጵያ ቡና በዋነኝነት በመግዛት ቻይና የምትጠቀስ ሲሆን ካለፈው ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ቡናን በመግዛት ከነበረችበት 33ኛ ደረጃ ተስፈንጥራ በአሁኑ ወቅት 4ተኛዋ ቡና ገዢ ሀገር ሆናለች። ባለፈው ዓመት ብቻ ኢትዮጵያ ወደ ቻይና ከ35 ሺህ ቶን በላይ ቡና መላኳን መረጃዎች ያሳያሉ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለፁት፤ በቡና ዘርፍ ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው በተሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ነው፡፡ በዚህም በየዓመቱ ለአለም ገበያ የሚቀርበውን የቡና ምርትና ጥራት በመጨመር ገቢውን ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡ በተያዘው 2018 በጀት ዓመትም ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለአለም ገበያ በማቅረብ 3 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ዘንድሮ የአለም የቡና ዋጋ 40 በመቶ መቀነሱን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ በዓመቱ የተያዘውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ጥራትን መሰረት ያደረገ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እስካሁንም ከ400 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለአለም ገበያ መቅረቡን ጠቅሰው በዓመቱ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን ገልጸዋል፡፡ በተለይም የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ የድህረ ምርት ጥራት አጠባበቅ ላይ በተሰራው ሰፊ ስራ በአለም ገበያ የኢትዮጵያ ቡና ተፈላጊነት መጨመሩን ተናግረዋል፡፡ የቡናን ጥራትና ምርታማነት የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎችን በመተግበርና በክልሎች ያሉ ተሞክሮዎችን በማስፋት በቀጣይም ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ እየተጫወተ ያለውን ሚና የማሳደግ ስራ በትኩረት እንደሚከናወን ገልጸዋል፡፡   የሲዳማ ክልል ቡና ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፋን ቃሬ በበኩላቸው፤ በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከ26 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን በተደረገ ጥረትም 24 ሺህ 100 ቶን ቡና ለማእከላዊ ገበያ መቅረቡን አስረድተዋል። አለም አቀፍ የቡና ዋጋ መቀነስና ሌሎች ጉዳዮችን በምክንያት አንስተው እንደ ሃገር በጥራት በመወዳደር በእቅዱ የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል። በቀጣይም የቡና ጥራት ማሻሻያ ፓኬጆች አተገባበርን በማጠናከር የቡና ጥራትና ምርታማነትን የማሳደግ ተግባር በትኩረት እንደሚከናወንም አመልክተዋል።
በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት እየተጠናቀቁ ናቸው
Jun 29, 2026 823
ነቀምቴ ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማቀላጠፍና የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት እየተጠናቀቁ መሆኑ ተገለጸ። በምስራቅ ወለጋ ዞን ዋዩ ቱቃ ወረዳ በ99 ሚሊየን ብር በላይ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። በፕሮጀክት ምረቃ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ለሜሳ አየለ እንደገለፁት፤ መንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍና የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው።   በዚህም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉት ፕሮጀክቶችም የስራ እድል የሚፈጥሩና የዞኑን የገቢ አቅም የሚያሳድጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምስራቅ ወለጋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ደሱ ለሚ በበኩላቸው፤ መንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ደረጃ በደረጃ ለመፍታት መስራቱን አንስተዋል።   ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናግረዋል። ለአገልግሎት ክፍት ከተደረጉት ፕሮጀክቶች መካከል የስራ እድልን ማስፋት የሚያስችሉ የመስሪያና የመሸጫ ቦታዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። በብልፅግና ፓርቲ የምስራቅ ወለጋ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቃዱ ገመዳ በበኩላቸው፤ መንግስት ለህብረተሰቡ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የገባውን ቃል ለመፈጸም በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   በዚህም እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመው ለዚህም የዛሬዎቹ ፕሮጀክቶች ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የዋዩ ቱቃ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አማኑኤል መኮንን በበኩላቸው ፤ከ99 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የከብት እርባታ ማእከል ፣ ድልድዮች ፣ መንገዶች ፣ የቡሳ ጎኖፋ እህል ማከማቻ መጋዘን እና ሌሎች ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን ገልጸዋል።   የልማት ፕሮጀክቶቹም ለማህበረሰቡ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡና የወረዳውን ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንደሚያሳልጡ ጠቁመዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዩኒቨርሲቲው የተሻሻሉ የወተት ላም ዝርያዎችን በማራባት ለአካባቢው አርሶ አደሮች እያከፋፈለ ነው
Jun 30, 2026 103
አምቦ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የተሻሻሉ የወተት ላሞች ዝርያ በማራባት የአካባቢው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆን የበኩሉን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ። በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ጉደር ማሞ መዘመር ካምፓስ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ዶክተር አማን ሪቂቱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን፣ በምርምር በማስደገፍ የተሻሻሉ የወተት ላሞችን በማራባት ለአካባቢው አርሶ አደሮች እንዲደርሱ እያደረገ ነው። ዩኒቨርሲቲው ከቶኬ ኩታዬ ወረዳ ጋር በመቀናጀት፣ ድጋፍ የሚገባቸውን የማኅበረሰብ ክፍሎች በመለየት የወተት ላሞቹ የሚቀርቡበትን ሁኔታ በማመቻቸት ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ይህም የአርሶ አደሮቹን ገቢ ከመጨመር ባለፈ፣ በአካባቢው የወተትና የወተት ተዋጽኦ በሰፊው ለገበያ እንዲቀርብ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ድረስ 15 ዝርያቸው የተሻሻለ የወተት ላሞች ለአካባቢው አርሶ አደሮች መስጠቱን ተናግረዋል። በካምፓሱ የወተት ከብት እርባታ ምርምር ቡድን መሪ አቶ ተሬሳ ተመስገን በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰቡን የወተት ምርት ለማሳደግ የሆሮ፣ ቦረና እና የውጪ አገር ዝርያ ያላቸው ላሞች ዝርያን በምርምር በማዳቀልና በማራባት የአካባቢው አርሶ አደሮች እያከፋፈለ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት በምርምር ዝርያቸው የተሻሻሉ 170 የወተት ላሞች እንደሚገኙ አንስተው፤ ከእነዚህም መካከል በዘንድሮው ዓመት 10 የሚሆኑትን ለአርሶ አደሮች ለማድረስ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በምዕራብ ሸዋ ዞን የቶኬ ኩታዬ ወረዳ አርሶ አደር ምስጋና ለታ እንደተናገሩት፤ ከዩኒቨርሲቲው ከተሰጣቸው የወተት ላም በቀን እስከ 15 ሊትር ወተት እያገኙ ነው። የወተት ምርቱን ለአካባቢው ሕብረተሰብ በማቅረብ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰቦቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እያስተዳደሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ዲጂታላይዝድ መደረጉ አገልግሎቶችን በሚፈለገው ልክ ተደራሽ ማድረግ እያስቻለ ነው
Jun 29, 2026 556
ባህር ዳር፤ ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የወሳኝ ኩነት ምዝገባ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ መደረጉ አገልግሎቶችን በሚፈለገው መልኩ ተደራሽ ማድረግ እያስቻለ መሆኑ የክልሉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ። የአገልግሎቱ ኃላፊ መዓዛ በዛብህ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በክልሉ የወሰኝ ኩነቶች መዝገባ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በመደረጉ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ፍትሃዊና ተደራሽ ለማድረግ እያስቻለ ነው ብለዋል። በበጀት ዓመቱ 982 ሺህ 800 የልደት፣ የሞት፣ የጉዲፈቻ፣ የጋብቻና ፍች ኩነቶችን ለመስጠት ታቅዶ ከእቅድ በላይ 107 በመቶ ማከናወን መቻሉን ጠቅሰዋል። የምዝገባ አገልግሎቱ ከሚሰጥባቸው ከ4 ሺህ የሚበልጡ ጣቢያዎች ውስጥ 570 የሚሆኑት በቴክኖሎጂ የተደራጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለውጤቱም ጠንካራ የቅንጅት ስራ ከመኖሩ ባለፈ በተለያዩ አማራጮች ለማህበረሰቡ የተሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች ተጠቃሽ መሆኑን ጠቁመዋል። የህብረተሰቡን የአገልግሎት እርካታ የማሳደግና የቴክኖሎጂ አሰራርን ተደራሽ ለማድረግና በተሻለ መልኩ ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የኩነቶች ምዝገባ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲደገፍ መደረጉ የመንግስትን ወጪ ከመቀነስ ባለፈ መረጃዎችን በጥራትና በፍጥነት ተደራሽ ማድረግ ማስቻሉን ጠቅሰዋል። በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተቀናጀ መንገድ በተሰራ ስራ ከ5 ሚሊየን በላይ ኩነቶችን መመዝገብ እንደተቻለም ኃላፊዋ አስታውቀዋል።
የዩኒቨርሲቲው የኢንኩቤሽን ማዕከል የፈጠራና ክህሎት ውጤቶችን የምናስተዋውቅበት ምቹ ምኅዳር ፈጥሮልናል 
Jun 28, 2026 887
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የኢንዱስትሪ ኢንኩቤሽን ማዕከል የቴክኖሎጂ ፈጠራና ክህሎት ውጤቶችን ለኢንዱስትሪዎች የሚያስተዋውቁበት ምቹ ምኅዳር እንደፈጠረላቸው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሙያተኞች ገለጹ። የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የፈጠራ ሙያተኞችን ከኢንዱስትሪዎችና አጋሮች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ የፈጠራ ሥራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ማስተዋወቂያ መድረክ ማካሄዱ ይታወቃል።   በመድረኩም በዩኒቨርሲቲው የኢንዱስትሪያል ኢንኩቤሽን ማዕከል በተማሪዎችና በተመራማሪዎች የተሰሩ የፈጠራና ክህሎት ውጤቶች ቀርበዋል። የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ከማል ኢብራሂም (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢንኩቤሽን ማዕከሉ ለተማሪዎችና የፈጠራ ሙያተኞች ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።   የማዕከሉ ዋና ዓላማ ተማሪዎች የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ፈጣሪና ኢንተርፕርነር የሚሆኑበትን ዓለም አቀፍ መደላድል መፍጠር መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም የዩኒቨርሲቲው የኢንዱስትሪ ኢንኩቤሽን ማዕከል ተማሪዎችን፣ ተመራማሪዎችንና ኢንዱስትሪዎች በአንድ ቦታ የሚገናኙበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንዳስቻለ አስረድተዋል። የስሪ ዲ ፕሪንቲንግ ዲጂታል ኮንስትራክሽን የቤት መሥሪያ ማሽን ያለሙት ዮሐንስ ረጋሳ (ዶ/ር)፤ ማዕከሉ የፈጠራ ባለቤቶችንና የኢንዱስትሪ አጋሮች በቀጥታ የሚገናኙበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።   ለዕይታ ያቀረቡት የስሪ ዲ ዲጂታል ኮንስትራክሽን ማሽንም በኮምፒውተር የታገዘ ዲዛይንን ወደ ማሽን ቋንቋ በመቀየር በውስን የሰው ሃይል ጊዜ ቆጣቢና ጥራት ያለው ግንባታን ማከናወን እንደሚያስችል ገልጸዋል። የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ የፈጠራ አቅምን መጎልበት የአሰራር ሥርዓቶችን በራስ አቅም በማሳለጥ ዘመናዊ ተግባራትን ለማከናወን ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል። ሌላኛው የፈጠራ ባለቤት ወጣት ሳሙኤል አለሙ በበኩሉ፤ በሀገር በቀል የምህንድስና ዕውቀት የለስላሳ መጠጦችን መሸጥና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ተንቀሳቃሽ የቬንዲንግ ማሽን ማልማቱን ገልጿል። የቬንዲንግ ማሽኑም የሁሉንም ባንኮች የክፍያ አማራጭና የደንበኞችን ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ በማንኛውም ሰዓት ያለአንዳች ኃይል መቆራረጥ ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ተናግሯል። ቬንዲንግ ማሽኑ ለትምህርትና ጤና ተቋማት ጭምር ተመራጭና ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጥ ነው ብሏል። ተማሪዎችም በትምህርት ቤት ቆይታቸው የሚያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት በማጎልበት ለሚስተዋሉ የቴክኖሎጂ ክፍተቶች መፍትሔ መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝቧል።
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 28, 2026 948
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። በኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ የፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚዎች ቁጥር ወደ 90 ሚሊየን ለማድረስ ግብ መቀመጡ ይታወቃል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በታህሳስ ወር ”ፋይዳ ለሴቶች” ሀገር አቀፍ የንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብርን አስጀምሯል። ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ከይረዲን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሴቶችን የዲጂታል አገልግሎቶች ተጠቃሚነት ለማላቅ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤትነትና ተደራሽነት በስፋት እየተሰራበት ይገኛል።   ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራምና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበርም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሴቶች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በእስካሁኑ ሂደት 26 ሚሊየን ሴቶችን የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ባለቤት በማድረግ የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተደራሽነትም የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል የሴቶችና ሕፃናት ምክትል ቢሮ ኃላፊ ሰሚራ ፋሪስ፤ በከተማና ገጠር የሚኖሩ የክልሉ ሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።   የሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤትነትም ሁለንተናዊ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። በአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዝና ጌታቸው በበኩላቸው፤ የሴቶችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤትነት ለማረጋገጥ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጭምር እየተሰራበት ነው ብለዋል።   በዚህም ከባድርሻ ተቋማት ጋር በመተባበር በተከናወነ ሥራ በ2018 ዓ.ም እስካሁን ድረስ ከ5 ሚሊየን በላይ የክልሉ ሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ማድረግ መቻሉን አስታውቀዋል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሴቶችና ሕፃናት ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊና የሴቶች ዘርፍ ኃላፊ ነጅሚያ ራህመቶ በበኩላቸው፤ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።   በዚህም የአደረጃጀቶችን ንቅናቄ በመጠቀም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሴቶችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ማድረግ እንደተቻለ አስረድተዋል። በጋምቤላ ክልል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አረየት ዑጁሉ በበኩላቸው፤ በክልሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ በማካሄድ ሴቶች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።   ይህም በተለያዩ አገልግሎቶች ላይ የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የልማት አካል እንዲሆኑ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስፖርት
የዓለም ዋንጫ 3ኛ ቀን የጥሎ ማለፍ መርሐ-ግብር፤ ኮትዲቯር ከኖርዌይ፣ ፈረንሳይ ከስዊድን እና ሜክሲኮ ከኢኳዶር
Jun 30, 2026 302
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል። ኮትዲቯር ከኖርዌይ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በዳላስ ስታዲየም ይጫወታሉ። በምድብ አምስት በስድስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው ኮትዲቯር በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብታለች። ኖርዌይ በምድብ ዘጠኝ በስድስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። የሰሜን አውሮፓዊቷ ሀገር ወደ ጥሎ ማለፉ ስትገባ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ነው። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የሀገራቱ አሸናፊ በቀጣይ ዙር ከብራዚል ጋር ይጫወታል። በሌላኛው መርሐ ግብር ፈረንሳይ ከስዊድን ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ላይ በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ፈረንሳይ በምድብ ዘጠኝ ሁሉንም ጨዋታዎቿን በማሸነፍ በዘጠኝ ነጥብ በመሪነት አጠናቃለች። ፈረንሳይ ወደ ጥሎ ማለፉ ስትገባ የአሁኑ ለ11ኛ ጊዜ ነው። ተጋጣሚዋ ስዊድን በአራት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ በምርጥ ሶስተኝነት ወደ 32 ዙር ገብታለች። በውድድሩ ተሳትፎ ታሪኳ ለጥሎ ማለፍ ስታልፍ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ለመጀመሪያ ጊዜ ይገናኛሉ። አሸናፊው ቡድን በቀጣዩ ዙር ከፓራጓይ ጋር ይገናኛል። ከዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሜክሲኮ ከኢኳዶር ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በሜክሲኮ ሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሜክሲኮ በምድብ አንድ በዘጠኝ ነጥብ የምድቡ መሪ በመሆን በውድድሩ ተሳትፎዋ ታሪክ ለ10ኛ ጊዜ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብታለች። ተጋጣሚዋ ኢኳዶር በምድብ አምስት አራት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ በምርጥ ሶስተኝነት ወደ ጥሎ ማለፍ ገብታለች። ሁለቱ ቡድኖች በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ጃፓን እና ኮሪያ ሪፐብሊክ እ.አ.አ በ2002 በጣምራ ባዘጋጁት 17ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በምድብ መርሐ ግብር ተገናኝተው ሜክሲኮ 2 ለ 1 አሸንፋለች። ሀገራቱ ከ24 ዓመታት በኋላ በጥሎ ማለፉ ተገናኝተዋል። ሜክሲኮ ወደ ጥሎ ማለፍ ስትሸጋገር ለ10ኛ ጊዜ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ተጋጣሚዋ ኢኳዶር ጥሎ ማለፍ ስትገባ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። የዛሬው ጨዋታ አሸናፊ 16 ውስጥ ከእንግሊዝ እና ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አሸናፊ ጋር ይጫወታል።
ሞሮኮ ኔዘርላንድስን በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈች
Jun 30, 2026 207
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የ32 ዙር ጥሎ ማለፍ ተጠባቂ መርሐ ግብር ሞሮኮ ኔዘርላንድስን በመለያ ምት አሸንፋለች። ማለዳ ላይ በተጠናቀቀው እና በሞንቴሬይ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኮዲ ጋፕኮ በ72ኛው ደቂቃ ግቧን አስቆጥሯል። የጋፕኮ ጎል በፈጣን የማጥቃት ሽግግር የተገኘ ሲሆን ክሬሴንሲዮ ሳመርቪል ለግቧ መቆጠር ምክንያት ሆኗል። ከግቡ መቆጠር በኋላ በቅርቡ በእርግዝና ወቅት ሁለተኛ ልጁን በሞት ያጣው ጋፕኮ ስሜቱን በማልቀስ ገልጿል። የ27 ዓመቱ ጋፕኮ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ሶስት አድርሷል። በአጠቃላይ በውድድሩ ስድስት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል። ጨዋታው በኔዘርላንድስ አሸናፊነት ተጠናቀቀ ሲባል ኢሳ ዲዮፕ በ91ኛው ደቂቃ በግንባሩ በመግጨት ያስቆጠረው ጎል ሞሮኮን አቻ አድርጓል። መደበኛው 90 ደቂቃ በአቻ ውጤት በመጠናቀቁ ምክንያት 30 ደቂቃ ተጨምሯል። በጭማሪ ሰዓት ግብ ባለመቆጠሩ ምክንያት ጨዋታው ወደ መለያ ምት አምርቷል። በዚህም ሞሮኮ በመለያ ምት 3 ለ 2 በማሸነፍ ወደ ጥሎ ማለፍ ገብታለች። ሞሮኮ በጨዋታው በኳስ ቁጥጥር እና የግብ እድሎችን በመፍጠር ተሽላ ተገኝታለች። ጨዋታው በታክቲክ የታጠረ ነበር ማለት ይቻላል። ውጤቱን ተከትሎ ሞሮኮ ወደ 16 ውስጥ ገብታለች። በቀጣዩ ዙር ከካናዳ ጋር ትገናኛለች። ሞሮኮ በ22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያ የአፍሪካ ሀገር መሆኗ የሚታወስ ነው። ኔዘርላንድስ የዓለም ዋንጫ ጉዞዋ 32 ውስጥ አብቅቷል።
አካባቢ ጥበቃ
በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በፍራፍሬ ልማት ላይ በመሳተፍ ውጤታማ ሆነናል
Jun 30, 2026 87
ባህር ዳር፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በፍራፍሬ ልማት ላይ በመሳተፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን አሳድገናል ሲሉ በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ። በክልሉ በክረምት ወቅት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተከናወነ ይገኛል። በመርሃ ግብሩም ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በማዘጋጀትና አርሶ አደሩን ተሳታፊ በማድረግ ከ261 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን ለመሸፈን እየተሰራ ነው። የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላው ለአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ለደን ልማት፣ ለእንስሳት መኖ፣ ለኢንዱስትሪዎች ግብዓትና መሰል ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተው ተከላ እየተከናወነ ይገኛል። በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ አንጉቲ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ምንይችል ወንድሜነህ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በብዙ ነገር ጠቅሞናል ብለዋል። በተለይም በአካባቢው በስፋት እየተካሄደ ባለው የክላስተር አቮካዶ ልማት ከምርት ሽያጭ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸውም ገልፀዋል። ቀደም ሲል በአካባቢው ጤፍ፣ ዳጉሳና በቆሎ በስፋት ይመረት እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ላይ አብዛኛው አርሶ አደር አቮካዶ እያለማ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆኗል ብለዋል። ሌላው የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ካሳሁን አበበ በበኩላቸው፤ የአቮካዶ ልማት ከሌሎች ሰብሎች በተሻለ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ገልፀዋል። የክላስተር የአቮካዶ ልማት አርሶ አደሩ እርስ በእርሱ እንዲረዳዳ ከማድረጉም በላይ የግብይት ሰንሰለቱን የተሳለጠ እንዳደረገው ተናግረዋል። ቀጣይም በአረንጓዴ ልማት የደን ሃብት ጥበቃና እንክብካቤ ባሻገር የጀመሩትን የአቮካዶ ልማት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ለመጀመሪያ ጊዜ በአቮካዶ ልማት ላይ መሳተፋቸውን የገለፁት ደግሞ የጥሩ ብርሃን ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር አየሁ ሙሉ ናቸው። ከመጋቢት ወር ጀምረው ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሰው፤ ከሰሞኑ በክላስተር ተደራጅተው ማልማት መጀመራቸውን ገልፀዋል። በክልሉ በክረምት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ25 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ የቡናና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች ተዘጋጅተው ተከላ እየተከናወነ ይገኛል።
ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለዓለም ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራዊ እርምጃዎቿን አጠናክራ ትቀጥላለች 
Jun 30, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለዓለም ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራዊ እርምጃዎቿን አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡን ያሳተፈው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በእንጦጦ ፓርክ በተካሄደው በዚህ መርሃ ግብር ላይ የየሀገራቱ አምባሳደሮች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ለዓለም ምሳሌ በሚሆን መልኩ በውጤታማነት እየተገበረች ትገኛለች።   መርሃ ግብሩ የተጎዱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ ከማድረግ ባለፈ፣ በስራ ዕድል ፈጠራና ዘላቂ ልማትን እውን በማድረግ ረገድ ተጠቃሽ ውጤቶች እያመጣ መሆኑንም አብራርተዋል። የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ የአረንጓዴ አሻራ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ፤ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ረገድ የምትጫወተውን ግንባር ቀደም ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። የአየር ንብረት ለውጥ አንድ ሀገር ብቻውን መፍትሔ ሊሰጠው የሚችለው ጉዳይ ባለመሆኑ በጋራ መስራት ወሳኝ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ የዛሬው የችግኝ ተከላም ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ጋር ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ለዱር እንስሳት ህልውና ዓይነተኛ ሚና እንዳለው አንስተዋል። ዛሬ የምንተክለው ችግኝ ብቻ ሳይሆን ለመጪው ትውልድ ተስፋም ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ለምግብነት እና ለገቢ ምንጭነት የሚውሉ ችግኞች በስፋት ይተከላሉ  
Jun 30, 2026 192
ጂንካ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኦሞ ዞን በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ለምግብነት እና ለገቢ ምንጭነት የሚውሉ ችግኞች በስፋት እንደሚተከሉ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የደቡብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ምንላርገው አዲሱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ የልማት ሥራዎችን ለማከናወን ዝግጅት ተደርጓል። በዚህም ለምግብነት እና ለገቢ ምንጭነት የሚውሉ ችግኞች በስፋት እንደሚተከሉ የተናገሩት ኃላፊው፤ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በዋናነት ፓፓያ፣ ማንጎ፣ ሞሪንጋ፣ አቮካዶ እንዲሁም ቡና በስፋት እንደሚተከል ገልጸዋል። በተራቆቱ አካባቢዎች ላይ የሚተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁና አካባቢውም እንዲያገግም የችግኝ እንክብካቤ ሥራው በስፋት እንደሚከናወንም ጠቁመዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከችግኝ ተከላ ባሻገር በአርብቶ አደር አካባቢዎች ህብረተሰቡን በማስተባበር የግጦሽ ሣር ከለላ እና የእንክብካቤ ሥራዎች በስፋት ይከናወናሉ። መርሃ ግብሩን ውጤታማ ለማድረግም በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች፣ አርሶና አርብቶ አደሮች እንዲሁም የመንግስት ሠራተኞችን ጨምሮ ከ100 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ለማሳተፍ ታቅዷል ብለዋል።   በዞኑ ማሌ ወረዳ በነታ ጫሊቲ ቀበሌ የሚኖሩት አርብቶ አደር እዮኤል ጋልሻ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በአካባቢው ከዚህ ቀደም በተከናወኑ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች የተጎዱ አካባቢዎች ጭምር አገግመው ምርት መስጠት ጀምረዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በተለያየ መንገድ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ገልጸው፣ በየዓመቱ ችግኞችን ከመትከል ባለፈ በችግኝ እንክብካቤ ሥራ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በወረዳው የአሸከር ቀበሌ ነዋሪ አርብቶ አደር ናስር ዶቄ በበኩላቸው፤ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ቡና እና ሞሪንግ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ ለመሆን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።   ከግብርና ባለሙያዎች የተሻለ ምርት የሚሰጡ ችግኞችን መውሰዳቸውን እና ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም ጠቁመዋል። በዞኑ ሐመር ወረዳ የቡስካ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ገሌ ዳሎ፤ በአካባቢው የቡስካ ተፈጥሯዊ ጥብቅ ደንን ከጉዳት ከመጠበቅ ባለፈ በአካባቢው ችግኝ በመትከል ሲንከባከቡ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርም የተጎዱ አካባቢዎችን በአረንጓዴ ለማልማት በሚሰሩ ሥራዎች ላይ ተሳትፎ ለማድረግ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል።
የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ውበትና ድምቀት የሚያስደንቅ ነው 
Jun 29, 2026 721
አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ውበትና ድምቀት የሚያስደንቅ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፤ ፕሮጀክቱ መዲናዋን የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋም፣ ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች እንዲሁም ዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን ስልታዊ ሽግግር የሚያፋጥን ታላቅ አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ 87 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት የሚሸፍንና 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከተማዋን ጽዱ ከማድረግ ባለፈ ለነዋሪዎቿ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል። የከተማ አስተዳደሩ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ባዘጋጀው የምስጋና መርሐ-ግብር ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ነዋሪዎችም ፕሮጀክቱን ጎብኝተዋል። አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ልማቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣቱንና ለከተማዋ ውበት ተጨማሪ ድምቀት መፍጠሩን በአድናቆት ገልጸዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል አቶ ፈድሉ ኢብራሂም፤ የቀበና ወንዝ ቀደም ሲል ለረጅም ዘመናት በቆሻሻ መጣያነቱና በማይመች ሁኔታው ይታወቅ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት የተከናወነው አስደናቂ የልማት ስራ ግን አካባቢውን በሚያስደንቅ ሁኔታ የቀየረው ሲሆን ይህም ትልቅ ደስታና እርካታ እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል። ቀደም ሲል ስሙ በክፉ ይነሳ የነበረው ይህ አካባቢ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ውብ መልክዓ ምድር መቀየሩ እንዳስደነቃት የተናገረችው ደግሞ እስራኤል አሸናፊ ናት።   በአሁኑ ወቅት ስፍራው ለህጻናትና ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ምቹ መጫወቻና የመዝናኛ ቦታ ሆኖ መዘጋጀቱ እንዳስደሰታት ተናግራለች። ወጣት ዳንኤል በበኩሉ፤ የቀበና ወንዝ ዳርቻ ቀደም ሲል አስቀያሚና ለጤና ጠንቅ የነበረ ስፍራ መሆኑን አስታውሶ ይህን ስፍራ ውብ ያደረጉ አመራሮች ትልቅ ምስጋና እንደሚገባቸው ተናግሯል።     ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ከድር ጃርሶ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአካባቢው ላይ በአጭር ጊዜ የታየው ለውጥ እጅግ አስደናቂ እይታን መፍጠሩን አንስተዋል። ይህ ስፍራ ቀደም ሲል በቆሻሻ ተሸፍኖ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን በሐይቅ፣ በታንኳና በአረንጓዴ ሥፍራ የተዋበ መሆኑንና አካባቢው ለኑሮ ምቹና ማራኪ ሆኖ መገንባቱን የጠቀሱት ደግሞ መቅደስ በቀለ ናቸው።   አካባቢውን ለረጅም ዓመታት የሚያውቁት አቶ አብደላ ኑሪ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል ስፍራው እጅግ ምቾት የማይሰጥና የሚያሳቅቅ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት የታየው ውበትና ልማት እጅግ አስገራሚ መሆኑን የጠቀሱት አስተያየት ሰጪው፤ ይህ ተግባር ለመንግስት ትልቅ ምስጋና የሚያሰጥ ድንቅ ስራ መሆኑን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 14241
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 9797
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 8615
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 8514
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
 ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች
Jun 29, 2026 1192
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • ምንድንነት የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም ‘አስም’ እንደሚባልም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የኪንታሮት ህመም እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? • ምልክቶች የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ጠቁመዋል። ምልክቶቹም በአብዛኛው በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ አስገንዝበዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር)፣ የእንስሳት አይነ ምድር ሽታዎች ለዚህኛው አስም አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን አስረድተዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑንም ተናግረዋል። • አጋላጭ (ለህመሙ መባባስ) መንስዔዎች አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የዓየር ብክለት፣ ጭስ)፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ዓይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? 👉ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎችዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ 👉 በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ 👉 በቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ ሙቀት የሚሰጡ መከላከያ ልብሶችን መልበስ፤ 👉 ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ • ሕክምናው የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የዓየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ከ 3 እስከ 10 በመቶ ያህሉ የዓለም ሕዝብ በአስም ተጠቂ መሆኑንም ጠቁመዋል። #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢዜአ #የጤና_ነገር  
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 1847
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ከተጽዕኖ ፈጣሪነትና ተደማጭነት መጎልበት እስከ የአኅጉር ድምጽ መሆን - የኢትዮጵያን ታላቅነት የገለጠው የዲፕሎማሲው ዘርፍ ስኬት  
Jun 25, 2026 2529
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቷ የፓን አፍካኒዝም ንቅናቄን በማንሳት አኅጉራዊ ተቋማት እንዲመሠረቱ ፊታውራሪ ከመሆን ጀምሮ ለጎረቤቶቿ ሰላም ጉልኅ ሚና ተጫውታለች፤ አሁንም ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔን እያሰረጸች በርካቶች እንዲጋሯት አድርጋለች። እንደ ሀገር ከለውጡ መንግሥት ወዲህ ከተገኙ በርካታ ትላልቅ ስኬቶች መካከል በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው አንዱ ነው። ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የለውጡ መንግሥት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ዋነኛ መለኪያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ነው። የኢትዮጵያ ሁኔታዎችን የማሰብ፣ የመፈለግና የመከወን ሂደት ንጥል (ለራስ ብቻ የሚል) ሳይሆን፤ በወንድማማችነት/እህትማማችነት ዕሳቤ በጋራ ማደግን ያነገበ ነው። ይህ ሂደቷም በበርካታ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ እንዲሁም አኅጉር አቀፍ ተቋማት ተወድሷል። በዚህም ሐሳቦቿ ቅቡል ሲሆኑ ተመልክተናል። ኢትዮጵያ የ#BRICS አባል መሆን መቻሏ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ይህም ተሰሚነቷን ያረጋገጠ ማስረጃ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ተያያዥ ጉዳዮች ዘርፈ-ብዙ ጥቅም በማስገኘት የበለጸገች ኢትየጵያን ዕውን የማድረግ ጉዞው ያፋጥናል። ወዲህ ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልና አፍሪካን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና መመረጧም የአኅጉሪቱ ድምጽ መሆኗን ይነግረናል። ዓለም አቀፍ ብሎም አኅጉር አቀፍ የሆኑ በርካታ ኮንፈረንሶችም በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እንዲካሄዱ መደረጉ አንድምታው ብዙ ነው። በብቃት ማስተናገዷ ደግሞ ሌላኛው ጥንካሬዋ። ሌላው የሀገራችንን የተጨበጠ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት የሚገልጽልን፤ የዓለም የዓየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን (COP32) እንድታዘጋጅ መመረጧ ነው። ይህን ትልቅ ዕድል በርካቶች ስለተመኙት አላገኙትም፤ ኢትዮጵያ ግን ዜጎቿን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባከናወነችው ያላሰለሰ ትጋት አግኝታዋለች። ግጭት ባለባቸው የቀጣናው ሀገራትም በመንግሥታቱ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት ሥር ከምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባለፈ፤ በግሏ የሰራችው ብዙ ነው። ከራሷ አልፋ ለጎረቤቶቿ ዘብ መሆኗ፤ በአብሮነት መኖርን እና በጋራ ማደግን በተግባር የገለጠች ሀገርም ያደርጋታል። ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ በሚለው ቅድሚያ ለሀገር በቀል ዕውቀቶች በሩን ክፍት ባደረገው ትጋቷም፤ በበርካታ የአኅጉሪቱ ሀገራት ዘንድ ምሥጋና አስችሯታል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲዋም በተለያዩ ሀገራት በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎቿን ከሀገራቱ እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመነጋገር በተሳካ ሁኔታ ልጆቿን ወደ ዕቅፏ መልሳለች፤ በቅርቡ በሳዑዲ ዓረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምኅረት ዐዋጅ እንዲሰጣቸው መደረጉ አንድ ማሳያ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን ጨምሮ በተለያዩ አኅጉራት በሚገኙ ሀገራት መሪዎችና ተወካዮች ዘንድ በስፋት የተመረጠችና የተጎበኘች ሀገር መሆኗን ማስታወስ ተገቢ ነው። ከጉብኝት ባለፈ ትላልቅ ስምምነቶችም የተፈራረመች መሆኗን ልብ ማለት ይገባል፤ ይህም የምታነሳውን ሐሳብ ገዥነትና የአፍሪካ መግቢያ በር መሆኗን ያሳያል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ መሆኑን መረዳት ይገባል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድርድር ሂደት የተጎናጸፈችው የዲፕሎማሲ ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መነቃቃት መፍጠሩንም ማጤን ያስፈልጋል። ይህ የተሳካው ሀገሪቱ ኢትዮጵያ መንገዷም የጋራ ልማትን የሰነቀ ዕውነት በመሆኑ ነው። በቀጣይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለአንዲት ሀገራቸው አምባሳደር በመሆን፤ የዲፕሎማሲውን ሥራ በይበልጥ ማገዝ ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ካልሠሩ ማን ለሀገራቸው ሊሠራ ይችላል?
እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል?
Jun 25, 2026 1738
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በዝምታ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት፤ የጨጓራ፣ አንጀትና ጉበት ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሚፍታህ ደሊል ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የጉበት ጤናን እንዴት መጠበቅ እንደሚቻል፣ ለጉበት ጤና መታወክ ስለሚያጋልጡ ጉዳዮች፣ ስለጉበት ስብ (ቅባት) እንዲሁም ሕክምናው ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል። · በሰው ልጅ ሕይዎት (ሠርካዊ እንቅስቃሴ) ውስጥ የጉበት ሚና ምንድን ነው? ዶክተር ሚፍታህ እንደገለጹት፤ ጉበት በሰውነታችን ውስጥ ኪሚገኙ ትላልቅ የውስጥ አካል ክፍሎች (ኦርጋኖች) አንዱ ነው። ከ1 ሺህ በላይ ተግባራትን የሚያከናውን ትልቁ እና ባተሌ የሆነ የአካል ክፍል መሆኑንም አስረድተዋል። የኪንታሮት በሽታ መንስዔ ይታወቃል? ካንሰር እንዴት ይከሰታል? · ለጉበት ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ይታወቃሉ? ለጉበት ህመም አጋላጭ ከሆኑ መንስዔዎች መካከል፤ ቫይረሶች (ሄፓታይትስ ቢ፣ ሄፓታይትስ ሲ) እንዲሁም አልኮል (ከፍተኛ መጠን ያለው አልኮል መጠጣት) መሆናቸውን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅት ደግሞ በስፋት የሚስተዋለው አጋላጭ መንስዔ የጉበት ስብ መጨመር መሆኑንም በአጽንዖት ገልጸዋል። በእኛ ሀገር ደረጃ ከሚከሰቱ የጉበት ህመሞች 50 በመቶው በሄፓታይትስ ቢ ምክንያት የሚከሰት ነው ይላሉ ዶክተር ሚፍታህ። ከ15 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የጉበት ህመም የሚከሰተው ደግሞ በአልኮል ምክንያት መሆኑን ነው ያስረዱት። እንዲሁም በሄፓታይትስ ሲ ምክንያት የሚከሰተው የጉበት ህመም ከላይ ከተገለጹት ቀጥሎ በሦስተኛነት እንደሚቀመጥም አመላክተዋል። አሁን አሁን ደግሞ ይላሉ ዶክተር ሚፍታህ፤ በሥራም ሆነ ለመዝናናት ለረጂም ሠዓታት መቀመጥን ተከትሎ የጉበት ስብ (ቅባት) በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋና ለጉበት ህመም እያጋለጠ መሆኑን አስገንዝበዋል። · የጉበት ፋት (ስብ፣ ቅባት) ለጉበት ህመም የሚያጋልጥበት ምክንያት ምንድን ነው? የጉበት ስብ በተለያዩ ሀገራት (በእኛም ሀገር በትላልቅ ከተሞች) በስፋት የሚከሰት ነው ያሉት ዶክተር ሚፍታህ፤ የጥናት ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከዓለም ሕዝብ 30 በመቶው (1/3ኛው ወይም ከ2 ቢሊየን በላይ ያህሉ) የጉበት ስብ ሊኖርበት ይችላል ይላሉ። በእርግጥ ሁሉም የጉበት ስብ ወደ ከፍተኛ የጉበት ቁስለት ይሸጋገራል ማለት እንዳልሆነ ገልጸው፤ የጉበት ስብ ካለባቸው መካከል ከ10 እስከ 15 በመቶ ያህሉ ብቻ ስቡ ከመብዛቱ የተነሳ ጉበቱን ማቁሰል እንደሚጀምር አስገንዝበዋል። ይህ ቁስለት ደግሞ እየዳነ እንደገና እያገረሸ ጠባሳ እየፈጠረ ይሄድና ጉበት ሥራውን ማከናወን የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ የጉበት መድከም ይከሰታል፤ ሰዎችም ጉዳት ይደርስባቸዋል ይላሉ። የጉበት ስብ መንስዔም፤ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ አለማድረግ (መቀመጥን ማዘውተር)፣ ፋስት ፉድ ማዘውተር (የተጠበሱ ምግቦች፣ በርገር፣ ችብስ፣ ዘይት የበዛባቸው ምግቦች) እንዲሁም ከፍተኛ ስኳር ያላቸው ለስላሳ መጠጦች፣ አልኮል መሆናቸውን አብራርተዋል። · የጉበት ስብን እንዴት መከላከል ይቻላል? የጉበት ስብ ከፍ እያለ ሲሄድ በአልትራሳውንድ እንደሚታይ (ትንሽ ከሆነ አይታም) የገለጹት ዶክተር ሚፍታህ፤ እስካሁን ክትባት እንደሌለው አረጋግጠዋል። ይህ ኬዝ እንቅስቃሴ ባለማድረግ፣ ኮምፒውተርም ሆነ ቴሌቪዥን ለማየት ረጂም ሠዓት በመቀመጥና በውፍረት መጨመር የሚከሰት መሆኑን ጠቁመው፤ መከላከያ መንገዱም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ (ቢያንስ በሳምንት እስከ 150 ደቂቃ በእግር መሄድ (ዎክ ማድረግ) ወይም በቀን ለ30 ደቂቃ ዎክ ማድረግ) መሆናቸውን ዘርዝረዋል። በተጨማሪም በፋብሪካ ፕሮሰስ የተደረጉ የታሸጉ ምግቦችን አለማዘውተር፣ ከስኳር ነጻ የሚሉ የሚበሉም ሆነ የሚጠጡ ነገሮችም ቢሆኑ በቀጥታም ባይሆን በሌላ መንገድ ጣፋጭ ስለሚኖራቸው አለማዘውተር፣ የተጠበሱ እንደ ችብስ እና መሰል ያሉ ምግቦችንም አለማዘውተር እንደሚገባ መክረዋል። ከልክ ያለፈ ውፍረት እንዳይኖር ማድረግም ለጉበት ስብ ተጋላጭነትን እንደሚቀንስ አስረድተዋል። · የጉበት በሽታ ምልክቶች እንደ ኬዙ ቢለያይም ጉበት 80 በመቶ ያህል ክፍሉ እስከሚጎዳ ምልክት ላያሳይ እንደሚችል ዶክተር ሚፍታህ ይገልጻሉ። 15 ወይም 10 በመቶ ጤናማ ክፍሉ ሲቀር (ከ85 በመቶ በላይ ክፍሉ በጣም ሲጎዳ) አንዳንድ ምልክቶች ሊያሳይ እንደሚችል ገልጸዋል። እነዚህ ምልክቶችም፤ ሆድ ላይ ውኃ መፍጠር (አሳይተስ)፣ ደም ማስመለስ መሆናቸውን እና በዚህ ወቅት የጉበት ንቅለ ተከላ ካልሆነ መፍትሔ እንደሌለው አንስተዋል። በአንጻሩ ግን፤ ‘አኪዩት ሄፓታይትስ’ የሚባለው ወይም አንድ ቫይረስ ጉበትን ሲያጠቃ ወዲያውኑ ሕክምና ይደረግለታል ሙሉ በሙሉም ይድናል ብለዋል።በዚህ ወቅት የሚየሳየው ምልክትም የዐይን ቢጫ መሆን፣ በቀኝ ደረት ሥር የውጋት ስሜት መኖር፣ ከፍተኛ ድካም መኖር፣ የምግብ ፍላጎት አለመኖር (ምግብ አስጠላኝ ማለት)፣ ማቅለሽለሽ እንዲሁም ማስመለስ መሆናቸውን አብራርተዋል። · የጉበት በሽታ አሳሳቢ ነው? የጉበት በሽታ በዓለም አቀፍ ደረጃም በተለያዩ ሀገራት ከ1 እስከ 10 ገዳይ (አሳሳቢ) ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል መሆኑን ዶክተር ሚፍታህ አስረድተዋል። በእኛ ሀገር ደረጃም የጉበት ካንሰር ከ3 እስከ 4 ገዳይ ተብለው ከሚጠቀሱ በሽታዎች መካከል መሆኑን ነው የጠቆሙት። በዓለም በየዓመቱ እስከ 3 ሚሊየን ሰዎች በጉበት በሽታ እንደሚሞቱ ገልጸው፤ ይህ አኃዝ አሳሳቢነቱን ያስረዳል ብለዋል። ምንም እንኳን ቀድሞ በሚወሰድ ክትባት (ለሄፓታይትስ ቢ) ከተከሰተ በኋላም በሚወሰድ መድኃኒት (ለሄፓታይትስ ሲ) አበረታች ውጤቶች ቢኖሩም፤ የጉበት ስብ (ቅባት) ግን በሀገራችንም ሆነ በዓለም ላይ በተለይም በከተማ ነዋሪዎች ዘንድ በስፋት እየተስተዋለ ያለ በመሆኑ አሳሳቢ ነው ብለዋል። · የጉበት በሽታ በተለይም በየትኞቹ የዕድሜ ክልሎች ላይ በስፋት ይከሰታል? የጉበት በሽታው ዓይነት በስፋት የሚከሰትበትን ዕድሜ እንደሚወስን ጠቁመው፤ በዚህም መሠረት ለምሳሌ፡- ሄፓታይትስ ቢ ከ30 ዓመት በታች ባሉ ሰዎች ላይ፣ ሄፓታይትስ ሲ ከ20 እስከ 40 ዓመት (አንዳንድ ጊዜ ከ40 ዓመት በላይ ባሉ ሰዎች ላይም ሊከሰት ይችላል)፣ የጉበት ስብ (ቅባት) ደግሞ ከ40 ዓመት በላይ ባሉ ሰዎች ላይ በስፋት እንደሚስተዋል ያስረዳሉ። · የጉበት በሽታን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? ዶክተር ሚፍታህ እንዳሉት የጉበት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የቻልባቸው የተለያዩ አማራጮች አሉ። ለምሳሌ፡- የሰውነት ክብደት (ውፍረት) ከልኩ እንዳያልፍ መቆጣጠር፣ ረጂም ሠዓት አለመቀመጥ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር፣ አልኮል አለመጠጣት (በቀን ከአንድ ቢራ በላይ መጠጣት ለጉበት ስብ ያጋልጣል)፣ ጣፋጭ ምግብና መጠጦችን መቀነስ (ጭራሽ አለመጠቀም ቢቻል)፣ ዘይት የበዛባቸውና የተጠባበሱ ምግቦችንም አለማዘውተር የሚሉትን አንስተዋል። በተጨማሪም በእኛ ሀገር ቀዳሚው የጉበት በሽታ ሄፓታይትስ ቢ መሆኑን በመግለጽ፤ ለዚህም ከ95 በመቶ በላይ የመከላከል ዐቅም ያለው ክትባት ስላለው ሦስት ጊዜ በመከተብ አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠዋል። · የሕክምና አማራጮች አሉት? ሄፓታይትስ ቢ ተከስቶ ጉበቱን ማቁሰል ከጀመረም የሚሰጥ ውጤታማ መድኃኒት መኖሩን አስታውቀዋል። ይህ መድኃኒት ምናልባት ዕድሜ ልክ ሊወሰድ ይችላል ነገር ግን ቁስለቱንም ሆነ ቫይረሱን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ነው ያሉት። ሄፓተይትስ ሲ ከሆነ ደግሞ በጣም ውጤታማ የሆነ ለሦስት ወር የሚሰጥ መድኃኒት አለ ብለዋል። ጠባሳ ከሆነ እና ከ85 በመቶ በላይ የሚሆነው የጉበት ክፍል ከተጎዳ (ከተበላሸ) ግን በውጭ ሀገር የጉበት ንቅለ ተከላ ማድረግ አስገዳጅ ይሆናል ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ ተላላፊ ካልሆኑ የጉበት በሽታዎች አንዱ እና አሁን በስፋት እየተስተዋለ ያለውን የጉበት ስብ (ቅባት) ጨምሮ የጉበት ጤናን ለመጠበቅ፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በየቀኑ ማድረግን መክረዋል። በዓመት አንድ ጊዜ የጤና ምርመራ በማድረግ ያሉበትን ሁኔታ ማወቅም ቢለመድ ሲሉ ይመክራሉ። በወቅቱ ከተደረሰብት የጉበት በሽታ መዳን እንደሚችል ገልጸው፤ በቸልተኝነት ወደ ተወሳሰበ ደረጃ ከፍ ካለ ግን እስከ ጉበት ካንሰር ሊደርስ እንደሚችልም አመላክተዋል።  
ትንታኔዎች
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 3895
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው  
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 4901
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ።   ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…! 
Jun 15, 2026 3324
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ! • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 8683
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። ‎ የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 5208
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 17912
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 10974
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 16732
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 92033
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 70846
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 51047
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 48605
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 35950
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 35461
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 34945
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 34093
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 92033
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 70846
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 51047
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 48605
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን አቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 1158
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 1769
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም