ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በአዲስ አበባ ከታቀደው በላይ ዜጎች የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠናን ለመውሰድ ተመዝግበዋል
Jun 16, 2026 20
አዲስ አበባ፤ሰኔ 9/2018(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በእቅድ ከተያዘው በላይ ዜጎች የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠናን ለመውሰድ መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታወቀ። በከተማዋ ከ809 ሺህ በላይ ዜጎች የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠናን እንዲወስዱ ለማድረግ ታቅዶ፥ ከ996 ሺህ በላይ ዜጎች ስልጠናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን ቢሮው ገልጿል። እስካሁን ባለው ሂደት ስልጠናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት ዜጎች መካከል ከ742 ሺህ የሚሆኑትም ስልጠናውን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት ወስደዋል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ምህዳር ውስጥ ንቁ ተሳታፊና ተወዳዳሪ ለመሆን በዲጂታል መሠረተ ልማትና በዲጂታል ክህሎት እየተዘጋጀች ነው። የዚህ ብሔራዊ ግብ አካል የሆነው የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ መርሃ ግብር ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ መጀመሩ ይታወሳል። በሦስት ዓመት ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ 5 ሚሊዮን ወጣቶች በኦንላይን የኮዲንግ ስልጠና እንዲወስዱ ዓላማ ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ ባስተላለፉት መልዕክት በመርሃ ግብሩ በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ስልጠናውን ማጠናቀቃቸውንና ይህ ስኬት የሕዝቡ ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የስማርት ሲቲ ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ቱሉ ጥላሁን ለኢዜአ እንዳሉት፥ የ5 ሚሊዮን ኮደሮች መርሃ ግብር የዲጂታል ክህሎትን የሚያሳድግ ነው። የኮደርስ ስልጠናዎች የዲጂታል ክህሎትን ከማሳደጋቸው በተጨማሪ የፈጠራ ሃሳብን የሚያጎለብቱና ቴክኖሎጂ ለማልማት የሚችሉበት እድል የሚፈጥር መሆኑንም ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ከ800 ሺህ በላይ የሰው ኃይልን ለማሰልጠን መታቀዱንና ጠቅሰው፥እስካሁን ባለው መረጃ ከ90 በመቶ በላይ ያህል ዜጎች ስልጠናቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልፀዋል። በከተማዋ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ እቅድን ለማሳካት ቢሮው ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑንም አንስተዋል። ቢሮው የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት የሚያጠናክሩ ሌሎች ዘመናዊ ስርዓቶችን ወደተግባር በማስገባት ስልጠና ለመስጠት ማቀዱን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የኮደርስ ሰልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ መታቀዱንና ይህንን ብሔራዊ ተልዕኮ ለማሳካትም ዜጎች በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
አርጀንቲና ከአልጄሪያ፣ ፈረንሳይ ከሴኔጋል – የዓለም ዋንጫው ወሳኝ ፍልሚያዎች
Jun 16, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የስድስተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በምድብ 10 የወቅቱ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ አርጀንቲና ከአልጄሪያ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በካንሳስ ሲቲ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል። ሁለቱ ቡድኖች በዓለም ዋንጫ መድረክ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም እ.አ.አ በ2007 ባደረጉት ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታ አርጀንቲና 4 ለ 3 አሸንፋለች። ለ19ኛ ጊዜ በዓለም ዋንጫው ተሳትፎ የምታደርገው አርጀንቲና የሶስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ናት። የወቅቱ የዋንጫ ባለቤትም ናት። የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጄሪያ በዓለም ዋንጫው ስትሳተፍ የአሁኑ ለአምስተኛ ጊዜ ነው። አልጄሪያ እ.አ.አ በ2014 በብራዚል በተካሄደው 20ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ደርሳ በጀርመን 2 ለ 1 ተሸንፋ ከውድድሩ የተሰናበተችበት አጋጣሚ በውድድሩ ታሪክ ትልቁ ውጤቷ ነው። የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ያነሳሉ ተብለው ከሚጠበቁት ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው አርጀንቲና ጨዋታውን የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት አግኝታለች። ተጋጣሚዋ አልጄሪያው በጨዋታው ላይ በቀላሉ እጅ ትሰጣለች ተብሎ አይጠበቅም። በምድብ ዘጠኝ ፈረንሳይ ከሴኔጋል ምሽት አራት ሰዓት በሜት ላይፍ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። እ.አ.አ በ2002 ጃፓን እና ኮሪያ ሪፐብሊክ በጣምራ ባዘጋጁት 17ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ላይ ቡድኖቹ ያደጉት ጨዋታ አይረሴ የታሪክ ክስተት የተስተናገደበት ነበር። እ.አ.አ በ1998 16ኛውን የዓለም ዋንጫ ራሷ አዘጋጅታ ሀገሯ ላይ ዋንጫውን ያስቀረችው ፈረንሳይ ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ ግምት ተሰጥቷታል። በሴኡል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሴኔጋል በፓፓ ቡባ ዲዮፕ የ30ኛ ደቂቃ ጎል ፈረንሳይን 1 ለ 0 በማሸነፍ ዓለምን ጉድ ያስባለ ድል አስመዘገበች። ሴኔጋል በወቅቱ እስከ ሩብ ፍጻሜ የደረሰች ሲሆን ፈረንሳይ ከምድቡ ማለፍ አለመቻሏ በወቅቱ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። ከዚህ ክስተት 24 ዓመታት ቆይታ በኋላ ሀገራቱ በድጋሚ የሚገናኙበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ፈረንሳይ በዓለም ዋንጫው ለ16ተኛ ጊዜ የምትሳተፍ ሲሆን ሁለት ጊዜ ዋንጫውን አንስታለች። በውድድሩ ላይ ለአራተኛ ጊዜ ተሳትፎዋን የምታደርገው ሴኔጋል ትልቁ ውጤቷ በ17ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ የደረሰችበት ነው። በሌሎች መርሐ ግብሮች በምድብ 10 ኦስትሪያ ከጆርዳን ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በሳንፍራንሲስኮ ቤይ ስታዲየም ይጫወታሉ። በምድብ ዘጠኝ ኢራቅ ከኖርዌይ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በቦስተን ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የወልዲያ ከተማ የኮሪደር ልማት ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት ከመሆን ባለፈ ምቹ የመዝናኛ ሥፍራ ፈጥሯል
Jun 16, 2026 42
ደሴ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በወልድያ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት ከመሆን ባለፈ ምቹ የመዝናኛ ሥፍራ መፍጠሩን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። በከተማዋ እየተከናወነ ካለው 18 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ 6 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ የሚታወቅ ነው። የኮሪደር ልማቱን በማስመልከት ኢዜአ በወልደያ ከተማ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ የልማት ሥራው ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ከመሆን ባለፈ ምቹ የመዝናኛ ስፍራ ፈጥሮላቸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ጠቅል ንጉሴ የኮሪደር ልማት ሥራው ትውልድን ታሳቢ አድርጎ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ ለልማት ሥራው ውጤታማነት የሚጠበቅባቸውን በመወጣት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማቱ ለወልዲያ ከተማ ተጨማሪ ውበት ከመሆን ባለፈ ለህብረተሰቡ ምቹና አማራጭ የመዝናኛ ስፍራ እየፈጠረ መምጣቱን ገልጸዋል። ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ ታሪኩ ሞገስ በበኩላቸው፣ በሌሎች ከተሞች በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ቁጭት ቢፈጠርባቸውም በአሁኑ ወቅት በከተማዋ በተከናወኑ የልማት ሥራዎች መካሳቸውን ተናግረዋል። "የዘመናት የልማት ጥያቄያችን መልስ አግኝቷል" ያሉት ነዋሪው፣ በተለይ የኮሪደር ልማቱ የወልድያ ከተማን ውበት አጉልቶ ከማውጣት ባለፈ ከተማዋን ለኑሮና ለመዝናኛነት ምቹ ማድረጉን ገልፀዋል። በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ለልማት ሥራ መፋጠን ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸው፣ በቀጣይም የአካባቢያቸውን ሰላም ከማጠናከር ባለፈ ለልማቱ ሲያደርጉት የነበረውን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። በወልዲያ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት ከመሆን ባለፈ ከተማዋ ለቱሪስት፣ ለኢንቨስትመንትና ለኑሮ ምቹ እንድትሆን አድርጓል ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ቸርነት እሸቴ ናቸው። በከተማዋ ቀደም ሲል የነበረው የአስፋልት መንገድ የተበላሸና ጠባብ በመሆኑ ተሽከርካሪ፣ ሰውና እንስሳት እየተጋፉ ሲጓዙ እንደነበር አስታውሰው፣ ይህም ለትራፊክ አደጋ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ብለዋል። የኮሪደር ልማቱ የተሽከርካሪ፣ የብስክሌት እና የእግረኛ መንገድን ከማካተቱ ባለፈ የአረንጓዴ ልማት፣ የመዝናኛ እና የልጆች መጫወቻን ጭምር አካቶ በመከናወኑ ችግሩ መፈታቱን ገልጸዋል። የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው እንዳሉት፣ የከተማውን ሰላም ከማረጋገጥ ባለፈ ህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። በከተማው 18 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንና ከዚህ ውስጥ 6 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትሩ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉን አመልክተዋል። ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው የኮሪደር ልማት ከስታድየም-ጎንደር በር፤ ከጎንደር በር- ሙጋድ፤ ከአዳጎ አደባባይ-ሙጋድ፤ ከአዳጎ አደባባይ -ፒያሳ እና - መነኸሪያ የተከናወኑ ልማቶችን ያካተተ እንደሆንም አስረድተዋል። ቀሪውን የኮሪደር ልማት ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ህብረተሰቡን ባሳተፈ አግባብ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ዱባለ ተናግረዋል።
በሀገር ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ረገድ የጀመርናቸውን ተግባራት አጠናክረን እንቀጥላለን - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 16, 2026 116
ሐረር፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- የሀገር ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ተግባራትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በሐረሪ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት አስታወቁ። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በተቋቋመበት መርህ መሠረት፣ በሀገራዊና ክልላዊ አበይት ጉዳዮች ላይ ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት በጋራ አጀንዳዎች ላይ አብሮ መስራት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው አካል ተደርጎ ይወሰዳል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም በተመሳሳይ መልኩ በልማት፣ በሰላምና በብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ የጋራ አቋም ማንጸባረቁ፣ በክልሉ ጤናማና ተቀራራቢ የፖለቲካ ባህልን ለማሳደግ እየተደረገ ስላለው ጥረት ማሳያ ነው። ከጋራ ምክር ቤቱ አባላት መካከል የሐረሪ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ሀዲድ) ተወካይ አቶ ሁሴን ሱሌይማን እንደገለጹት፤ በፓርቲዎች መካከል የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሩም ለሀገርና ለክልል ልማት እንዲሁም ለሰላም በትብብር እየተከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክረው ይቀጥላሉ። በተለይም የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ዘላቂ ምላሽ እንዲያገኝ በሚደረገው ጥረትና በሌሎችም ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ዙሪያ የማይደራደሩ መሆናቸውን አቶ ሁሴን አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል። የሀገርን ሰላም ለማወክና ብሔራዊ ጥቅምን ለማሳጣት ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ አካላትን አፍራሽ ተግባር ፓርቲያቸው በንቃት እየተከታተለ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሁሴን፤ እነዚህን ኃይሎች ከህዝብ ጋር በመተባበር በቁርጠኝነት እንደሚታገሏቸውም አስታውቀዋል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ተወካይ ሀሰነት ሙሜ በበኩላቸው፤ ፓርቲው የኢትዮጵያን ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን አስቀድሞ የሚሄድና ለሀገር አፍራሽ የሆኑ ተግባራትን የሚታገል ነው። "ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማት ያለ ልዩነት በቅንጅት እንሰራለን" ያሉት ወይዘሮ ሃሰነት፤ በተለይም ለሀገር ጠንቅ የሆኑ የጽንፈኞችን ተግባር የጋራ ምክር ቤቱ በንቃት እየተከታተለና በአቋም ደረጃ የሚታገል መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በመሰባሰብና በመወያየት በክልሉ ዘላቂ ልማት፣ ሰላምና ሁለተናዊ እድገት ላይ ፓርቲያቸው በቅንጅት እየሰራ ነው ያሉት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ አባልና የኢዜማ ተወካይ ማህሌት ዘውዱ ናቸው። ሀገርን ለማተራመስና ብሔራዊ ጥቅምን ለማሳጣት የሚሞክሩ ሃይሎች ከባለፈው ክስተት ያልተማሩና ለህዝብ የማያስቡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ድርጊት እንዲታቀቡና በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር ለህዝብ ጥቅም መረጋገጥ ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባቸው ተናግረዋል። በክልሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ በተለያዩ የልማት መስኮችና የሀገርን ጥቅም በሚያስከብሩ ተግባራት ላይ የፖለቲካ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው በጋራ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዳይሬክተር አቶ ሀሰን አብዲ ናቸው። የክልሉን ልማትና ሰላም በማጽናት ሀገሪቱን ወደፊት የማስኬድ ተግባርን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አክለዋል።
በባሌ ዞን ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እየተደረገ ነው
Jun 16, 2026 77
ሮቤ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል። ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ሥራ ላይ በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥሪ ማቅረባቸውም ይታወሳል። በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ስኬታማ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ሥራ እየተሠራ ይገኛል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሙአዊያ ፉአድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ባለፉት ዓመታት ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በተከናወነው መርሃ ግብር የተራቆተ መሬትን መልሶ በደን በመሸፈን ረገድ ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል። ይህንን ተግባር ለማስቀጠልም በመጪው ክረምት የሚተከሉ ከ229 ሚሊዮን የሚበልጡ ችግኞችን በመንግስት፣ በማህበራትና በግል የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች የማዘጋጀቱ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። እስካሁን ከ211 ሚሊዮን በላይ ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን፣ 194 ሚሊዮን የሚሆኑ የመትከያ ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውንና ቀሪው ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በዞኑ በችግኝ ማፍያ ጣቢያዎቹ በአብዛኛው ሀገር በቀልና ሌሎች የውጭ ዝርያ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በጽህፈት ቤቱ የተፋሰስና የደን ልማት ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ ኦሊቃ ናቸው። አካባቢው በዓመት ሁለት ጊዜ የበልግና የክረምት ዝናብ የሚያገኝ በመሆኑ ተከላውም ይህንን ስነ-ምህዳር ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ከመጋቢት መጀመሪያ እስከ ሚያዝያ መጨረሻ በጣለው የበልግ ዝናብ 105 ሚሊዮን የሚሆኑ ችግኞች መተከላቸውንና ቀሪው ተከላ በሐምሌ ወር እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል ጥድ፣ ኮሶ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ፣ ግራቪሊያ፣ የእንስሳት መኖና የጥላ ዛፎች የሚገኙበት ሲሆን፣ 8 በመቶ ያህሉ ደግሞ ለሰው ምግብነት የሚውሉ አትክልትና ፍራፍሬ ናቸው ብለዋል። የሐረና ቡሉቅ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ሐሰን፤ በወረዳው የህዝቡን የድርቅ ተጋላጭነት ለመከላከል የተጀመረው ጥረት ህብረተሰቡን በማሳተፍ መጠናከሩን ገልጸዋል። በዚህም በ60 በመቶው የበልግ ዝናብ በመጠቀም፣ ለተከላ ከተዘጋጁ 25 ሚሊዮን ችግኞች መካከል ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውን መትከል መቻሉን አስታውቀዋል። ከወረዳው ነዋሪዎች መካከል አርብቶ አደር ጀማል ሁሴን በሰጡት አስተያየት፤ የድርቅ ተጋላጭነትን ለመቀነስ ችግኝ መትከል የህልውና ጉዳይ መሆኑን ካለፉት ዓመታት ተጨባጭ ውጤት መረዳታቸውንና በዘንድሮው መርሃ ግብር ላይ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። በባሌ ዞን ባለፈው የክረምት ወቅት ከተተከሉ ከ245 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መካከል በተደረገ ቆጠራ 87 በመቶው ጸድቆ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ፖለቲካ
በሀገር ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ረገድ የጀመርናቸውን ተግባራት አጠናክረን እንቀጥላለን - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 16, 2026 116
ሐረር፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- የሀገር ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ተግባራትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በሐረሪ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት አስታወቁ። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በተቋቋመበት መርህ መሠረት፣ በሀገራዊና ክልላዊ አበይት ጉዳዮች ላይ ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት በጋራ አጀንዳዎች ላይ አብሮ መስራት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው አካል ተደርጎ ይወሰዳል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም በተመሳሳይ መልኩ በልማት፣ በሰላምና በብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ የጋራ አቋም ማንጸባረቁ፣ በክልሉ ጤናማና ተቀራራቢ የፖለቲካ ባህልን ለማሳደግ እየተደረገ ስላለው ጥረት ማሳያ ነው። ከጋራ ምክር ቤቱ አባላት መካከል የሐረሪ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ሀዲድ) ተወካይ አቶ ሁሴን ሱሌይማን እንደገለጹት፤ በፓርቲዎች መካከል የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሩም ለሀገርና ለክልል ልማት እንዲሁም ለሰላም በትብብር እየተከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክረው ይቀጥላሉ። በተለይም የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ዘላቂ ምላሽ እንዲያገኝ በሚደረገው ጥረትና በሌሎችም ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ዙሪያ የማይደራደሩ መሆናቸውን አቶ ሁሴን አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል። የሀገርን ሰላም ለማወክና ብሔራዊ ጥቅምን ለማሳጣት ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ አካላትን አፍራሽ ተግባር ፓርቲያቸው በንቃት እየተከታተለ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሁሴን፤ እነዚህን ኃይሎች ከህዝብ ጋር በመተባበር በቁርጠኝነት እንደሚታገሏቸውም አስታውቀዋል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ተወካይ ሀሰነት ሙሜ በበኩላቸው፤ ፓርቲው የኢትዮጵያን ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን አስቀድሞ የሚሄድና ለሀገር አፍራሽ የሆኑ ተግባራትን የሚታገል ነው። "ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማት ያለ ልዩነት በቅንጅት እንሰራለን" ያሉት ወይዘሮ ሃሰነት፤ በተለይም ለሀገር ጠንቅ የሆኑ የጽንፈኞችን ተግባር የጋራ ምክር ቤቱ በንቃት እየተከታተለና በአቋም ደረጃ የሚታገል መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በመሰባሰብና በመወያየት በክልሉ ዘላቂ ልማት፣ ሰላምና ሁለተናዊ እድገት ላይ ፓርቲያቸው በቅንጅት እየሰራ ነው ያሉት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ አባልና የኢዜማ ተወካይ ማህሌት ዘውዱ ናቸው። ሀገርን ለማተራመስና ብሔራዊ ጥቅምን ለማሳጣት የሚሞክሩ ሃይሎች ከባለፈው ክስተት ያልተማሩና ለህዝብ የማያስቡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ድርጊት እንዲታቀቡና በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር ለህዝብ ጥቅም መረጋገጥ ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባቸው ተናግረዋል። በክልሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ በተለያዩ የልማት መስኮችና የሀገርን ጥቅም በሚያስከብሩ ተግባራት ላይ የፖለቲካ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው በጋራ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዳይሬክተር አቶ ሀሰን አብዲ ናቸው። የክልሉን ልማትና ሰላም በማጽናት ሀገሪቱን ወደፊት የማስኬድ ተግባርን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አክለዋል።
በባህር ዳር ከተማ የሰላምና ጸጥታ ሥራዎችን በማስቀጠል የህዝብን ኑሮ ለማሻሻል የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ
Jun 15, 2026 898
ባህር ዳር፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ በማህበረሰቡ ተሳትፎ የሚከናወኑ የሰላምና ጸጥታ ሥራዎችን በማስቀጠል የህዝቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ። የባህር ዳር ከተማ አመራሮች የተሳተፉበት በልማትና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት ባህርዳርን በመሰረተ ልማት በማዘመን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ተመራጭ ከተማ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። በማህበረሰቡ ተሳትፎ የከተማዋን ሰላምና ልማት በማጠናከር የህዝብን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል። በተለይም የከተማዋን ማህበረሰብ በማሳተፍ የተከናወኑ የሰላምና የህግ ማስከበር ሥራዎች ለሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠሩ ገልጸዋል። የሰላሙ መጠናከር የኮሪደር ልማት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የስማርት ሲቲ ትግበራ እና ሌሎች ሰፋፊ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን አስችሏል ብለዋል። ይህም ከተማዋን ለኢንቨስትመንት፣ ለንግድ፣ ለቱሪዝምና ለኑሮ ምቹ በማድረግ የነዋሪውን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እንደሚያስችል አስረድተዋል። ማህበረሰቡም በጠቅላላ ምርጫው ድምጹን ከመስጠት ባለፈ ለምርጫው ሰላማዊነትና ስኬት ያደረገው አስተዋጽኦ ለሰላምና ልማት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳያል ብለዋል። በቀጣይም ህዝቡ በከተማዋ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ላይ የሚያደርገውን ንቁ ተሳትፎ በማሳደግ ለዘላቂ የብልጽግና ጉዞ የሚጠበቅበትን መወጣት አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል። የከተማ አስተዳደሩም በቀጣዮቹ 90 ቀናት የክረምት ሥራዎችን በላቀ ደረጃ በመፈጸምና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በመፍታት በጊዜ የለኝምመንፈስ ሊሰራ እንደሚገባ ምክትል ከንቲባው አሳሰበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ሃላፊ አቶ ጊዜው ታከለ እንዳሉት፣ በየደረጃው ያለው አመራር ዋነኛ ትኩረቱ ህዝብን በሰላምና በልማት ተጠቃሚ ማድረግ ነው። ለዚህም ህዝባዊነትን በመላበስ ቀልጣፋ፣ ፍትሐዊና ተአማኒነት ያለው አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት መሰራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደርና የክፍለ ከተሞች አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ማረጋገጥ የሚቻለው ችግሮችን በምክክር በመፍታትና መግባባት በመፍጠር ነው - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 15, 2026 722
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን ፈተናዎች ለመሻገርና ዘላቂ ጥቅሟን ለማስከበር ዋናው መንገድ ችግሮችን በምክክር መፍታትና ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ቆይተው፣ በሰላማዊ መንገድ ወደ ማህበረሰቡ ከተቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ጋር በአዳማ ከተማ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል። ውይይቱ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ የቀድሞ ታጣቂዎቹ አጀንዳዎቻቸውን ለኮሚሽኑ የሚያስረክቡም ይሆናል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመድረኩ እንደገለጹት፣ ወጣቶች ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ያሏቸውን ጥያቄዎች በአጀንዳ መልክ ቀርጸው ወደ ሀገራዊ ምክክሩ ማምጣታቸውን አድንቀዋል። ጥያቄዎችን ይዞ ወደ ምክክር መምጣት፣ ለችግሮች በጋራ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ትልቁን በር እንደሚከፍትም ገልጸዋል። የትኛውም ፍላጎትና ጥያቄ በመሳሪያ ሳይሆን በውይይት፣ በመነጋገርና በመመካከር መግባባት ላይ የሚደረስበት መሆኑን ወጣቶች ሊገነዘቡ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ማረጋገጥ የሚቻለው መሳሪያ ይዞ ጫካ ውስጥ በመግባት የወጣትነት እድሜን መስዋዕት በማድረግ ሳይሆን፣ የሀገሪቱን ችግሮች በፊት ለፊት ውይይትና ምክክር በጋራ በመፍታት መሆኑን አንስተዋል። የኮሚሽኑ ዋና ዓላማም ለማንም ወገን አድሎ ሳይደረግ፣ ሁሉም አካላት በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው ሀሳብ ለሀሳብ እንዲመካከሩ በማድረግ ለችግሮች ዘላቂ እልባት መፈለግና በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር መሆኑን አስረድተዋል። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚዳንት የሰላም ጉዳዮች አማካሪ ብርጋዴር ጄነራል ኃይሉ ጎንፋ በበኩላቸው፣የትኛውንም አጀንዳ በሰላማዊ መንገድ በመደማመጥ መፍታት መቻል ትልቅ እሴት መሆኑን አብራርተዋል። ማህበረሰቡ በየትኛውም ሁኔታ ሰላም እንዲደፈርስ አይፈልግም ያሉት ብርጋዴር ጄነራሉ፣ ልጆቹ ከነፍጥ ይልቅ የሰለጠነ ፖለቲካን እንዲለማመዱ ጽኑ ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል። የሰላም መንገድ ሁሉንም አሸናፊ በማድረግ ወጣቶች የነገዋን ሀገር ለመገንባት አሻራቸውን የሚያሳርፉበት መሆኑንም ጠቅሰዋል። ይህ ዓይነቱ በምክክር ላይ የተመሰረተ አካሄድ ትልቁ የትግል ማዕቀፍ መሆን እንደሚገባ በማንሳት፥ ሀገራዊ ፋይዳውም የላቀ ነው ብለዋል።
በዞኑ ማህበረሰቡን በማሳተፍ እየተከናወኑ ያሉ ዘላቂ ሰላምን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን የማስቀጠል ተግባራት ይጠናከራሉ
Jun 15, 2026 661
መተማ፣ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ):-በምዕራብ ጎንደር ዞን ማህበረሰቡን በማሳተፍ እየተከናወኑ ያሉ ዘላቂ ሰላምን የማረጋገጥና የተጀመሩ የልማት ስራዎችን የማስቀጠል ተግባራትን አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ የዞኑ አመራሮች ገለጹ። የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ከየወረዳው ከተወጣጡ አስተዳዳሪዎችና ከንቲባዎች ጋር በወቅታዊ የፀጥታና የልማት ስራዎች ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄደዋል። በወቅቱም የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ እንደገለጹት፤ በዞኑ ላለው ለውጥ፣ ዕድገትና አስተማማኝ ሰላም ዋነኛው ባለቤትና አጋዥ ህብረተሰቡ ነው። ዞኑ ሰፊ የኢንቨስትመንት እና የልማት ቀጠና መሆኑን ጠቅሰው የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ለሀገር ኢኮኖሚም ጭምር ወሳኝ ሚና እንዳለው አንስተዋል። "ባለፉት ጊዜያት ከህዝባችን ጋር በመቀናጀት በርካታ ፈተናዎችን ማለፍ ችለናል" ያሉት አስተዳዳሪው፣በቀጣይም ይኸው ህዝባዊ ትስስር ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እሸቴ ሙላው እንዳሉት፤ ሰላምን ለማስፈንና ልማትን ለማፋጠን ከህዝቡ ጋር መወያየትና አብሮ መስራት ይጠበቃል። አርሶ አደሩ ያለምንም ስጋትና በነፃነት ምርቱን ማምረት እንዲችል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማጠናከር ቀዳሚ ተግባር መሆኑን አብራርተዋል። ከአጎራባች አካባቢዎች ጋር ያለውን ሰላማዊ ትስስር ለማጥበቅና የወንጀል ድርጊቶችን በጋራ ለመግታት ከህብረተሰቡ የሚገኘው ጥቆማና ድጋፍ ከፍተኛ በመሆኑ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራም አንስተዋል። የመተማ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ግዛት ሰረፀ በበኩላቸው፣ ወረዳው በተፈጥሮ ሀብት የበለፀገ፣ ሰፊ የእርሻ መሬት ያለበት በመሆኑ ይህን ሀብት ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ሰላምን ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም በየቀበሌው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች ጋር የቅርብ ግንኙነት በመፍጠር የፀጥታ ስጋቶችን በጋራ የመከላከል ስራ በተጠናከረ ሁኔታ እየተተገበረ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በየደረጃው ለመመለስ በትኩረት እንደሚሰሩም አመራሮቹ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አርዓያ የሚሆን በቴክኖሎጂ የታገዘ ሰላማዊና የተሳካ ምርጫ ማካሄዷ የሚደነቅ ነው
Jun 15, 2026 819
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አርዓያ የሚሆን በቴክኖሎጂ የታገዘ ሰላማዊና የተሳካ ምርጫ ማካሄዷ የሚደነቅ መሆኑን በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩመር ራይ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ ያሉ አህጉራዊና ቀጣናዊ ተቋማት የምርጫ ታዛቢዎችን በማሰማራት ገለልተኛና ዲሞክራሲያዊነቱን የመሰከሩለት ጠቅላላ ምርጫ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ በምርጫው የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችም የተሳተፉ ሲሆን 55 የሲቪል ማህበራትን ያቀፈው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሳታፊ፣ ነጻና ዲሞክራሲያዊ መሆኑን መታዘቡን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የጸጥታ፣ የፍትሕና የዲሞክራሲ ተቋማት ምርጫውን በገለልተኝነትና በተቋማዊ ብቃት እንዲካሄድ ማስቻላቸውን መታዘቡን አረጓግጧል፡፡ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩመር ራይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት የተሳካ ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዳቸውን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምርጫው በፊት አሳታፊ ምርጫ እንደሚካሄድ በገቡት ቃል መሰረት መንግሥት ለምርጫው ዲሞክራሲያዊነት ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አድንቀዋል። ምርጫው በርካታ ኢትዮጵያውያን ድምጻቸውን የሰጡበት፣ የሴቶችና የወጣቶች የነቃ ተሳትፎ የታየበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ ያሉ አህጉራዊና ቀጣናዊ ተቋማት የምርጫ ታዛቢዎችን በማሰማራት ምርጫው ሰላማዊና ፍትሐዊ መሆኑን ማረጋገጣቸውም የምርጫውን ዴሞክራሲያዊነት የሚያሳይ መሆኑን በአድናቆት ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ከእጩዎችና መራጮች ምዝገባ ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ለአፍሪካውያን አርዓያ የሚሆን ነፃ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ማካሄድ ችላለች ነው ያሉት። የአፍሪካ ጉዳይ በአፍሪካውያን መፈታት አለበት ያሉት አምባሳደሩ፤ በኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ የአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ ታዛቢዎች መሰማራታቸው የዚህ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን የመገንባት ሂደት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ነው
Jun 15, 2026 757
ባህርዳር፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስፈን የሚያስችል የፀጥታ ኃይል እየተገነባ መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) ገለፁ። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ደህንነት አፈፃፀምን የሚገመግምና በቀጣይ ሁለት ወራት በሚከናወኑ ተግባራት ዕቅድ ዙሪያ የሚመክር መድረክ በባህር ዳር እየተካሄደ ነው። በመድረኩም የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በክልሉ ዘላቂ ሰላምን የመገንባት ሂደት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ይገኛል። ባለፋት ጊዜያት የፀጥታ ሃይሉ በተቀናጀ መንገድ በተሰራ ህግ የማስከበር ተግባር በክልሉ ሰላም ማስፈን መቻሉን ገልፀዋል። በዚህም በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙና የክልሉን ብሎም የሀገሪቱ ሰላም መሆን የማይዋጥላቸው ፀረ-ሰላም ኃይሎች የክልሉን ብሎም የሀገርን ሰላም አደጋ ላይ ለመጣል የተደረገውን ሙከራ ማክሸፍ እንደተቻለ አንስተዋል። በተለይም እነዚህ የህዝብና የሀገር ጠላት የሆኑ ፅንፈኛ ቡድኖች ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍ በተቀናጀ መንገድ ያደረጉትን ጥረት የፀጥታ ኃይሉ በላቀ ብቃት ማምከን መቻሉን ተናግረዋል። ፖሊስና ሌሎች የፀጥታ አባላት በጥምረት በሰሩት ስራም ምርጫው እንዳይካሄድ የተደረጉ ሙከራዎችን ሙሉ በሙሉ በማክሸፍ ምርጫው በስኬት እንዲከናወን ማድረጋቸውን አብራርተዋል። የፀጥታ ኃይሉ ህዝባዊነትን በተላበሰ መንገድ ባካሄደው ርብርብም ከምርጫ በፊት፣ በምርጫ ወቅትና ከምርጫ በኋላ ሊፈፀም የታሰበን አጥፊ ድርጊት ሊያመክን እንደቻለም አክለዋል። ምርጫው በስኬት እንዲከናወን የፀጥታ ኃይሉ ለተወጣው ኃላፊነት አመስግነው፤ በቀጣይም ሰላምን የማስጠበቁ ተግባር በላቀ ቁርጠኝነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በመድረኩ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የተቋሙ አመራሮች እየተሳተፋ ሲሆን የምርጫ ደህንነት አፈፃፀምና የቀጣይ ሁለት ወራት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።
የፌዴራል መንግሥት የትግራይን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል የወሰደውን ቁርጠኝነት የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ራሱን ለዕኩይ ዓላማ ለማደራጀት ተጠቅሞበታል
Jun 15, 2026 818
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦የፌዴራል መንግሥት የትግራይ ክልልን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል የወሰደውን ቁርጠኝነት ህልውናው ያከተመው ህገወጡ የቀድሞ የሕወሓት ቡድን ራሱን ለዕኩይ ዓላማ ለማደራጀት እንደተጠቀመበት አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) ገለጹ። የትግራይ ክልልን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የቀድሞው ሕወሓት የቀድሞ ሊቀ መንበር የነበሩት አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የፌዴራል መንግሥት ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት የትግራይ ክልልን ጊዜያዊ አስተዳደር በማዋቀር ሰብዓዊ ድጋፍና መልሶ ግንባታን ለማፋጠን ከፍተኛ በጀት መድቦ ሲሰራ ቆይቷል። ሆኖም ጦርነት ናፋቂው የቀድሞ ሕወሓት ፅንፈኛ ቡድን የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት ቢፈርምም አደገኛና ህገወጥ ወታደራዊ አቅም እየገነባ መቀጠሉን አመልክተዋል። የፌዴራል መንግሥቱ የዘላቂ ሰላምና ልማት ግንባታ ጥረቶች እንዳይሳኩ ጽንፈኛው የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ተደጋጋሚ የማደናቀፍ ተግባራትን እየፈጸመ መሆኑን አስረድተዋል። የትግራይ ክልል ወጣቶችን ለአስገዳጅ ወታደራዊ አፈሳና ምልመላ በመዳረግ ስጋት እንዲያንዣብብ ማድረጉን በመጥቀስ፥ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በፅንፈኛ ቡድኑ አማካኝነት የሰላም ስምምነቱ ሲደናቀፍ በዝምታ መመልከቱን አውስተዋል። የቀድሞ ሕወሃት ቡድን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን ለክልሉ ሕዝብ ዘላቂ ሰላምና ልማት ግንባታ ከመጠቀም ይልቅ ራሱን ለማደራጀትና የጥፋት ዓላማውን ለማሳካት በጊዜ መግዣነት ተጠቅሞበታል ብለዋል። የቡድኑ አመራሮችም ከውጪ ጠላት በሚሰጣቸው ትዕዛዝ መሰረት ሕጻናትን ከወላጆቻቸው በመንጠቅ ጭምር አዲስ ኃይል አደራጅተው ወደ ዳግም ግጭት ለመግባት የተሳሳተ አቅጣጫ እየተከተሉ መሆኑን አስረድተዋል። የክልሉ ሕዝብም ልጆቹን ከግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ ለመታደግ ከክልሉ ውጭ ወደሚገኙ አካባቢዎችና በውጭ ሀገራት ጭምር በማሸሽ የቡድኑን ሕገ-ወጥ ድርጊት አጥብቆ እየተቃወመ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ፅንፈኛ ቡድን በመሰላቸት ተስፋ የቆረጡ ነባር ታጣቂዎችም ለቀው በመውጣት ቡድኑን መዋጋት መጀመራቸውን አንስተዋል። የቀድሞ ሕወሓት ፅንፈኛ አካላት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የተቋቋመውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ ግጭት የሚያስከትል መዘዝ እየፈጠሩ መሆናቸውን አብራርተዋል። በሀገር ውስጥና በውጭ ዓለማት የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች፣ሌሎች ኢትዮጵያውያንና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የዚህን ፅንፈኛ ቡድን ሕገወጥ እንቅስቃሴ አጥብቀው ሊያወግዙ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የሀሳብ ልዩነቶችንና ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ የስልጡንነት መገለጫ ነው
Jun 15, 2026 757
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦የሀሳብ ልዩነቶችንና ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ የስልጡንነት መገለጫ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ቆይተው በሰላማዊ መንገድ ወደ ማህበረሰቡ ከተቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ጋር በአዳማ ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመድረኩ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የቀድሞ ታጣቂዎቹ ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ወደ ሰላማዊ መንገድ ለመመለስ የወሰኑትን ውሳኔ አድንቀዋል። የሀሳብ ልዩነቶችንና ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ የስልጡንነት መገለጫ ነው ያሉ ሲሆን፣ በሀገሪቱ ዘላቂ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በሰላም መመካከርና መነጋገር ብቸኛው አማራጭ መሆኑን ገልጸዋል። ኮሚሽኑ ዋናውን ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚያካሂድ መግለጹ ይታወቃል። ለዚህም በተለያዩ ምዕራፎች ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል አሳታፊና አካታች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ ማከናወኑም ይታወቃል። ኮሚሽኑ በክልሎች፣ በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በወረዳዎች እንዲሁም በውጭ ሀገራት ከሚኖሩ ዜጎች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ ማካሄዱም አይዘነጋም።
ፖለቲካ
በሀገር ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ረገድ የጀመርናቸውን ተግባራት አጠናክረን እንቀጥላለን - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 16, 2026 116
ሐረር፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- የሀገር ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ተግባራትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በሐረሪ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት አስታወቁ። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በተቋቋመበት መርህ መሠረት፣ በሀገራዊና ክልላዊ አበይት ጉዳዮች ላይ ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት በጋራ አጀንዳዎች ላይ አብሮ መስራት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው አካል ተደርጎ ይወሰዳል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም በተመሳሳይ መልኩ በልማት፣ በሰላምና በብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ የጋራ አቋም ማንጸባረቁ፣ በክልሉ ጤናማና ተቀራራቢ የፖለቲካ ባህልን ለማሳደግ እየተደረገ ስላለው ጥረት ማሳያ ነው። ከጋራ ምክር ቤቱ አባላት መካከል የሐረሪ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ሀዲድ) ተወካይ አቶ ሁሴን ሱሌይማን እንደገለጹት፤ በፓርቲዎች መካከል የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሩም ለሀገርና ለክልል ልማት እንዲሁም ለሰላም በትብብር እየተከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክረው ይቀጥላሉ። በተለይም የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ዘላቂ ምላሽ እንዲያገኝ በሚደረገው ጥረትና በሌሎችም ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ዙሪያ የማይደራደሩ መሆናቸውን አቶ ሁሴን አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል። የሀገርን ሰላም ለማወክና ብሔራዊ ጥቅምን ለማሳጣት ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ አካላትን አፍራሽ ተግባር ፓርቲያቸው በንቃት እየተከታተለ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሁሴን፤ እነዚህን ኃይሎች ከህዝብ ጋር በመተባበር በቁርጠኝነት እንደሚታገሏቸውም አስታውቀዋል። የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ተወካይ ሀሰነት ሙሜ በበኩላቸው፤ ፓርቲው የኢትዮጵያን ልማት፣ ሰላምና ብሔራዊ ጥቅምን አስቀድሞ የሚሄድና ለሀገር አፍራሽ የሆኑ ተግባራትን የሚታገል ነው። "ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማት ያለ ልዩነት በቅንጅት እንሰራለን" ያሉት ወይዘሮ ሃሰነት፤ በተለይም ለሀገር ጠንቅ የሆኑ የጽንፈኞችን ተግባር የጋራ ምክር ቤቱ በንቃት እየተከታተለና በአቋም ደረጃ የሚታገል መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በመሰባሰብና በመወያየት በክልሉ ዘላቂ ልማት፣ ሰላምና ሁለተናዊ እድገት ላይ ፓርቲያቸው በቅንጅት እየሰራ ነው ያሉት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ አባልና የኢዜማ ተወካይ ማህሌት ዘውዱ ናቸው። ሀገርን ለማተራመስና ብሔራዊ ጥቅምን ለማሳጣት የሚሞክሩ ሃይሎች ከባለፈው ክስተት ያልተማሩና ለህዝብ የማያስቡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ድርጊት እንዲታቀቡና በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር ለህዝብ ጥቅም መረጋገጥ ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባቸው ተናግረዋል። በክልሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ በተለያዩ የልማት መስኮችና የሀገርን ጥቅም በሚያስከብሩ ተግባራት ላይ የፖለቲካ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው በጋራ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዳይሬክተር አቶ ሀሰን አብዲ ናቸው። የክልሉን ልማትና ሰላም በማጽናት ሀገሪቱን ወደፊት የማስኬድ ተግባርን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አክለዋል።
በባህር ዳር ከተማ የሰላምና ጸጥታ ሥራዎችን በማስቀጠል የህዝብን ኑሮ ለማሻሻል የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ
Jun 15, 2026 898
ባህር ዳር፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ በማህበረሰቡ ተሳትፎ የሚከናወኑ የሰላምና ጸጥታ ሥራዎችን በማስቀጠል የህዝቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ። የባህር ዳር ከተማ አመራሮች የተሳተፉበት በልማትና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት ባህርዳርን በመሰረተ ልማት በማዘመን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ተመራጭ ከተማ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። በማህበረሰቡ ተሳትፎ የከተማዋን ሰላምና ልማት በማጠናከር የህዝብን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል። በተለይም የከተማዋን ማህበረሰብ በማሳተፍ የተከናወኑ የሰላምና የህግ ማስከበር ሥራዎች ለሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠሩ ገልጸዋል። የሰላሙ መጠናከር የኮሪደር ልማት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የስማርት ሲቲ ትግበራ እና ሌሎች ሰፋፊ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን አስችሏል ብለዋል። ይህም ከተማዋን ለኢንቨስትመንት፣ ለንግድ፣ ለቱሪዝምና ለኑሮ ምቹ በማድረግ የነዋሪውን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እንደሚያስችል አስረድተዋል። ማህበረሰቡም በጠቅላላ ምርጫው ድምጹን ከመስጠት ባለፈ ለምርጫው ሰላማዊነትና ስኬት ያደረገው አስተዋጽኦ ለሰላምና ልማት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳያል ብለዋል። በቀጣይም ህዝቡ በከተማዋ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ላይ የሚያደርገውን ንቁ ተሳትፎ በማሳደግ ለዘላቂ የብልጽግና ጉዞ የሚጠበቅበትን መወጣት አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል። የከተማ አስተዳደሩም በቀጣዮቹ 90 ቀናት የክረምት ሥራዎችን በላቀ ደረጃ በመፈጸምና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በመፍታት በጊዜ የለኝምመንፈስ ሊሰራ እንደሚገባ ምክትል ከንቲባው አሳሰበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ሃላፊ አቶ ጊዜው ታከለ እንዳሉት፣ በየደረጃው ያለው አመራር ዋነኛ ትኩረቱ ህዝብን በሰላምና በልማት ተጠቃሚ ማድረግ ነው። ለዚህም ህዝባዊነትን በመላበስ ቀልጣፋ፣ ፍትሐዊና ተአማኒነት ያለው አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት መሰራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደርና የክፍለ ከተሞች አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ማረጋገጥ የሚቻለው ችግሮችን በምክክር በመፍታትና መግባባት በመፍጠር ነው - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 15, 2026 722
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን ፈተናዎች ለመሻገርና ዘላቂ ጥቅሟን ለማስከበር ዋናው መንገድ ችግሮችን በምክክር መፍታትና ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ቆይተው፣ በሰላማዊ መንገድ ወደ ማህበረሰቡ ከተቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ጋር በአዳማ ከተማ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል። ውይይቱ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ የቀድሞ ታጣቂዎቹ አጀንዳዎቻቸውን ለኮሚሽኑ የሚያስረክቡም ይሆናል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመድረኩ እንደገለጹት፣ ወጣቶች ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ያሏቸውን ጥያቄዎች በአጀንዳ መልክ ቀርጸው ወደ ሀገራዊ ምክክሩ ማምጣታቸውን አድንቀዋል። ጥያቄዎችን ይዞ ወደ ምክክር መምጣት፣ ለችግሮች በጋራ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ትልቁን በር እንደሚከፍትም ገልጸዋል። የትኛውም ፍላጎትና ጥያቄ በመሳሪያ ሳይሆን በውይይት፣ በመነጋገርና በመመካከር መግባባት ላይ የሚደረስበት መሆኑን ወጣቶች ሊገነዘቡ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ማረጋገጥ የሚቻለው መሳሪያ ይዞ ጫካ ውስጥ በመግባት የወጣትነት እድሜን መስዋዕት በማድረግ ሳይሆን፣ የሀገሪቱን ችግሮች በፊት ለፊት ውይይትና ምክክር በጋራ በመፍታት መሆኑን አንስተዋል። የኮሚሽኑ ዋና ዓላማም ለማንም ወገን አድሎ ሳይደረግ፣ ሁሉም አካላት በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው ሀሳብ ለሀሳብ እንዲመካከሩ በማድረግ ለችግሮች ዘላቂ እልባት መፈለግና በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር መሆኑን አስረድተዋል። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚዳንት የሰላም ጉዳዮች አማካሪ ብርጋዴር ጄነራል ኃይሉ ጎንፋ በበኩላቸው፣የትኛውንም አጀንዳ በሰላማዊ መንገድ በመደማመጥ መፍታት መቻል ትልቅ እሴት መሆኑን አብራርተዋል። ማህበረሰቡ በየትኛውም ሁኔታ ሰላም እንዲደፈርስ አይፈልግም ያሉት ብርጋዴር ጄነራሉ፣ ልጆቹ ከነፍጥ ይልቅ የሰለጠነ ፖለቲካን እንዲለማመዱ ጽኑ ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል። የሰላም መንገድ ሁሉንም አሸናፊ በማድረግ ወጣቶች የነገዋን ሀገር ለመገንባት አሻራቸውን የሚያሳርፉበት መሆኑንም ጠቅሰዋል። ይህ ዓይነቱ በምክክር ላይ የተመሰረተ አካሄድ ትልቁ የትግል ማዕቀፍ መሆን እንደሚገባ በማንሳት፥ ሀገራዊ ፋይዳውም የላቀ ነው ብለዋል።
በዞኑ ማህበረሰቡን በማሳተፍ እየተከናወኑ ያሉ ዘላቂ ሰላምን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን የማስቀጠል ተግባራት ይጠናከራሉ
Jun 15, 2026 661
መተማ፣ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ):-በምዕራብ ጎንደር ዞን ማህበረሰቡን በማሳተፍ እየተከናወኑ ያሉ ዘላቂ ሰላምን የማረጋገጥና የተጀመሩ የልማት ስራዎችን የማስቀጠል ተግባራትን አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ የዞኑ አመራሮች ገለጹ። የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ከየወረዳው ከተወጣጡ አስተዳዳሪዎችና ከንቲባዎች ጋር በወቅታዊ የፀጥታና የልማት ስራዎች ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄደዋል። በወቅቱም የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ እንደገለጹት፤ በዞኑ ላለው ለውጥ፣ ዕድገትና አስተማማኝ ሰላም ዋነኛው ባለቤትና አጋዥ ህብረተሰቡ ነው። ዞኑ ሰፊ የኢንቨስትመንት እና የልማት ቀጠና መሆኑን ጠቅሰው የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ለሀገር ኢኮኖሚም ጭምር ወሳኝ ሚና እንዳለው አንስተዋል። "ባለፉት ጊዜያት ከህዝባችን ጋር በመቀናጀት በርካታ ፈተናዎችን ማለፍ ችለናል" ያሉት አስተዳዳሪው፣በቀጣይም ይኸው ህዝባዊ ትስስር ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እሸቴ ሙላው እንዳሉት፤ ሰላምን ለማስፈንና ልማትን ለማፋጠን ከህዝቡ ጋር መወያየትና አብሮ መስራት ይጠበቃል። አርሶ አደሩ ያለምንም ስጋትና በነፃነት ምርቱን ማምረት እንዲችል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማጠናከር ቀዳሚ ተግባር መሆኑን አብራርተዋል። ከአጎራባች አካባቢዎች ጋር ያለውን ሰላማዊ ትስስር ለማጥበቅና የወንጀል ድርጊቶችን በጋራ ለመግታት ከህብረተሰቡ የሚገኘው ጥቆማና ድጋፍ ከፍተኛ በመሆኑ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራም አንስተዋል። የመተማ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ግዛት ሰረፀ በበኩላቸው፣ ወረዳው በተፈጥሮ ሀብት የበለፀገ፣ ሰፊ የእርሻ መሬት ያለበት በመሆኑ ይህን ሀብት ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ሰላምን ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም በየቀበሌው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች ጋር የቅርብ ግንኙነት በመፍጠር የፀጥታ ስጋቶችን በጋራ የመከላከል ስራ በተጠናከረ ሁኔታ እየተተገበረ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በየደረጃው ለመመለስ በትኩረት እንደሚሰሩም አመራሮቹ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አርዓያ የሚሆን በቴክኖሎጂ የታገዘ ሰላማዊና የተሳካ ምርጫ ማካሄዷ የሚደነቅ ነው
Jun 15, 2026 819
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አርዓያ የሚሆን በቴክኖሎጂ የታገዘ ሰላማዊና የተሳካ ምርጫ ማካሄዷ የሚደነቅ መሆኑን በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩመር ራይ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ ያሉ አህጉራዊና ቀጣናዊ ተቋማት የምርጫ ታዛቢዎችን በማሰማራት ገለልተኛና ዲሞክራሲያዊነቱን የመሰከሩለት ጠቅላላ ምርጫ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ በምርጫው የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችም የተሳተፉ ሲሆን 55 የሲቪል ማህበራትን ያቀፈው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሳታፊ፣ ነጻና ዲሞክራሲያዊ መሆኑን መታዘቡን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የጸጥታ፣ የፍትሕና የዲሞክራሲ ተቋማት ምርጫውን በገለልተኝነትና በተቋማዊ ብቃት እንዲካሄድ ማስቻላቸውን መታዘቡን አረጓግጧል፡፡ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩመር ራይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት የተሳካ ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዳቸውን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምርጫው በፊት አሳታፊ ምርጫ እንደሚካሄድ በገቡት ቃል መሰረት መንግሥት ለምርጫው ዲሞክራሲያዊነት ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አድንቀዋል። ምርጫው በርካታ ኢትዮጵያውያን ድምጻቸውን የሰጡበት፣ የሴቶችና የወጣቶች የነቃ ተሳትፎ የታየበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ ያሉ አህጉራዊና ቀጣናዊ ተቋማት የምርጫ ታዛቢዎችን በማሰማራት ምርጫው ሰላማዊና ፍትሐዊ መሆኑን ማረጋገጣቸውም የምርጫውን ዴሞክራሲያዊነት የሚያሳይ መሆኑን በአድናቆት ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ከእጩዎችና መራጮች ምዝገባ ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ለአፍሪካውያን አርዓያ የሚሆን ነፃ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ማካሄድ ችላለች ነው ያሉት። የአፍሪካ ጉዳይ በአፍሪካውያን መፈታት አለበት ያሉት አምባሳደሩ፤ በኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ የአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ ታዛቢዎች መሰማራታቸው የዚህ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን የመገንባት ሂደት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ነው
Jun 15, 2026 757
ባህርዳር፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስፈን የሚያስችል የፀጥታ ኃይል እየተገነባ መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) ገለፁ። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ደህንነት አፈፃፀምን የሚገመግምና በቀጣይ ሁለት ወራት በሚከናወኑ ተግባራት ዕቅድ ዙሪያ የሚመክር መድረክ በባህር ዳር እየተካሄደ ነው። በመድረኩም የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በክልሉ ዘላቂ ሰላምን የመገንባት ሂደት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ይገኛል። ባለፋት ጊዜያት የፀጥታ ሃይሉ በተቀናጀ መንገድ በተሰራ ህግ የማስከበር ተግባር በክልሉ ሰላም ማስፈን መቻሉን ገልፀዋል። በዚህም በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙና የክልሉን ብሎም የሀገሪቱ ሰላም መሆን የማይዋጥላቸው ፀረ-ሰላም ኃይሎች የክልሉን ብሎም የሀገርን ሰላም አደጋ ላይ ለመጣል የተደረገውን ሙከራ ማክሸፍ እንደተቻለ አንስተዋል። በተለይም እነዚህ የህዝብና የሀገር ጠላት የሆኑ ፅንፈኛ ቡድኖች ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍ በተቀናጀ መንገድ ያደረጉትን ጥረት የፀጥታ ኃይሉ በላቀ ብቃት ማምከን መቻሉን ተናግረዋል። ፖሊስና ሌሎች የፀጥታ አባላት በጥምረት በሰሩት ስራም ምርጫው እንዳይካሄድ የተደረጉ ሙከራዎችን ሙሉ በሙሉ በማክሸፍ ምርጫው በስኬት እንዲከናወን ማድረጋቸውን አብራርተዋል። የፀጥታ ኃይሉ ህዝባዊነትን በተላበሰ መንገድ ባካሄደው ርብርብም ከምርጫ በፊት፣ በምርጫ ወቅትና ከምርጫ በኋላ ሊፈፀም የታሰበን አጥፊ ድርጊት ሊያመክን እንደቻለም አክለዋል። ምርጫው በስኬት እንዲከናወን የፀጥታ ኃይሉ ለተወጣው ኃላፊነት አመስግነው፤ በቀጣይም ሰላምን የማስጠበቁ ተግባር በላቀ ቁርጠኝነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በመድረኩ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የተቋሙ አመራሮች እየተሳተፋ ሲሆን የምርጫ ደህንነት አፈፃፀምና የቀጣይ ሁለት ወራት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።
የፌዴራል መንግሥት የትግራይን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል የወሰደውን ቁርጠኝነት የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ራሱን ለዕኩይ ዓላማ ለማደራጀት ተጠቅሞበታል
Jun 15, 2026 818
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦የፌዴራል መንግሥት የትግራይ ክልልን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል የወሰደውን ቁርጠኝነት ህልውናው ያከተመው ህገወጡ የቀድሞ የሕወሓት ቡድን ራሱን ለዕኩይ ዓላማ ለማደራጀት እንደተጠቀመበት አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) ገለጹ። የትግራይ ክልልን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የቀድሞው ሕወሓት የቀድሞ ሊቀ መንበር የነበሩት አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የፌዴራል መንግሥት ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት የትግራይ ክልልን ጊዜያዊ አስተዳደር በማዋቀር ሰብዓዊ ድጋፍና መልሶ ግንባታን ለማፋጠን ከፍተኛ በጀት መድቦ ሲሰራ ቆይቷል። ሆኖም ጦርነት ናፋቂው የቀድሞ ሕወሓት ፅንፈኛ ቡድን የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት ቢፈርምም አደገኛና ህገወጥ ወታደራዊ አቅም እየገነባ መቀጠሉን አመልክተዋል። የፌዴራል መንግሥቱ የዘላቂ ሰላምና ልማት ግንባታ ጥረቶች እንዳይሳኩ ጽንፈኛው የቀድሞ ሕወሓት ቡድን ተደጋጋሚ የማደናቀፍ ተግባራትን እየፈጸመ መሆኑን አስረድተዋል። የትግራይ ክልል ወጣቶችን ለአስገዳጅ ወታደራዊ አፈሳና ምልመላ በመዳረግ ስጋት እንዲያንዣብብ ማድረጉን በመጥቀስ፥ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በፅንፈኛ ቡድኑ አማካኝነት የሰላም ስምምነቱ ሲደናቀፍ በዝምታ መመልከቱን አውስተዋል። የቀድሞ ሕወሃት ቡድን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን ለክልሉ ሕዝብ ዘላቂ ሰላምና ልማት ግንባታ ከመጠቀም ይልቅ ራሱን ለማደራጀትና የጥፋት ዓላማውን ለማሳካት በጊዜ መግዣነት ተጠቅሞበታል ብለዋል። የቡድኑ አመራሮችም ከውጪ ጠላት በሚሰጣቸው ትዕዛዝ መሰረት ሕጻናትን ከወላጆቻቸው በመንጠቅ ጭምር አዲስ ኃይል አደራጅተው ወደ ዳግም ግጭት ለመግባት የተሳሳተ አቅጣጫ እየተከተሉ መሆኑን አስረድተዋል። የክልሉ ሕዝብም ልጆቹን ከግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ ለመታደግ ከክልሉ ውጭ ወደሚገኙ አካባቢዎችና በውጭ ሀገራት ጭምር በማሸሽ የቡድኑን ሕገ-ወጥ ድርጊት አጥብቆ እየተቃወመ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ፅንፈኛ ቡድን በመሰላቸት ተስፋ የቆረጡ ነባር ታጣቂዎችም ለቀው በመውጣት ቡድኑን መዋጋት መጀመራቸውን አንስተዋል። የቀድሞ ሕወሓት ፅንፈኛ አካላት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የተቋቋመውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ ግጭት የሚያስከትል መዘዝ እየፈጠሩ መሆናቸውን አብራርተዋል። በሀገር ውስጥና በውጭ ዓለማት የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች፣ሌሎች ኢትዮጵያውያንና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የዚህን ፅንፈኛ ቡድን ሕገወጥ እንቅስቃሴ አጥብቀው ሊያወግዙ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የሀሳብ ልዩነቶችንና ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ የስልጡንነት መገለጫ ነው
Jun 15, 2026 757
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦የሀሳብ ልዩነቶችንና ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ የስልጡንነት መገለጫ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ቆይተው በሰላማዊ መንገድ ወደ ማህበረሰቡ ከተቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ጋር በአዳማ ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመድረኩ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የቀድሞ ታጣቂዎቹ ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ወደ ሰላማዊ መንገድ ለመመለስ የወሰኑትን ውሳኔ አድንቀዋል። የሀሳብ ልዩነቶችንና ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ የስልጡንነት መገለጫ ነው ያሉ ሲሆን፣ በሀገሪቱ ዘላቂ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በሰላም መመካከርና መነጋገር ብቸኛው አማራጭ መሆኑን ገልጸዋል። ኮሚሽኑ ዋናውን ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚያካሂድ መግለጹ ይታወቃል። ለዚህም በተለያዩ ምዕራፎች ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል አሳታፊና አካታች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ ማከናወኑም ይታወቃል። ኮሚሽኑ በክልሎች፣ በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በወረዳዎች እንዲሁም በውጭ ሀገራት ከሚኖሩ ዜጎች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ ማካሄዱም አይዘነጋም።
ማህበራዊ
የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ዲጅታል ከማድረግ ባለፈ በብቁ ባለሙያዎች አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ ነው
Jun 16, 2026 119
ባህር ዳር፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ) ፡-የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ዲጅታል ከማድረግ ባለፈ በእውቀትና ክህሎት በብቁ ባለሙያዎች የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ መሆኑን የአማራ ክልል የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ገለጸ። በክልሉ የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የሪፎርም ድጋፍና ክትትል ዳይሬክተር አቶ እንዳላማው ይታይህ፤ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙ በአገልግሎት አሰጣጥና ተቋማት ውጤታማ እንዲሆኑ ከማድረግ አንፃር ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግቧል ብለዋል። በሪፎርሙ የሰራተኛው የመፈፀም አቅም፣ ነፃና ገለልተኛ ተቋም በመፍጠርና ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ረገድ እመርታ የተመዘገበበት መሆኑን ተናግረዋል። የመንግስትን አገልግሎት አሰጣጥ ዲጅታላይዝ በማድረግ ሂደት ሰራተኛውን ለላቀ አፈፃፀም በማብቃትም ብዙ ስኬቶች ተገኝተዋል ብለዋል። በመሆኑም የአገልግሎት አሰጣጥን ዲጅታል ከማድረግ ባለፈ በእውቀትና ክህሎት በብቁ ባለሙያዎች የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ ገንዘብ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ደሳለኝ አለምነህ፤ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በመተግበር የሚጨበጥ ውጤት ስለመታየቱ ተናግረዋል። የሰራተኛውን የስራ ባህል በመቀየር ቀልጣፋ፣ ዘመናዊና በዲጅታል አሰራር የታገዘ አገልገሎት እየተሰጠ መሆኑን አንስተዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አባይ መንግስቴ፤ በተቋማት የሚስተዋሉ የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት በውጤታማነት መቀጠሉን ገልጸዋል። የፖሊሲ ማሻሻያዎችን በማድረግ ከዘመኑ ጋር የሚራመድ የዲጅታል አገልግሎት እየተስፋፋ በመምጣቱና ለዚህ ብቁና ዝግጁ የሆነ የሰው ሃይል ማፍራት መቻሉ ለስኬቱ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሕክምና ቱሪዝም መዳረሻ የሚያደርጋትን መሠረት እየገነባች ነው
Jun 16, 2026 305
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት የሕክምና ቱሪዝም ማዕከል የሚያደርጋትን መሠረት እየገነባች መሆኑን የኢትዮጵያና የምሥራቅ አፍሪካ ጤና ክብካቤ ፌዴሬሽኖች ፕሬዝዳንት ዶክተር ማርቆስ ፈለቀ ገለጹ። የኢትዮጵያና ምሥራቅ አፍሪካ ጤና ክብካቤ ፌዴሬሽኖች ፕሬዝዳንት ዶክተር ማርቆስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የሕክምና ቱሪዝም ማዕከል መሆን የሚያስችል አቅም ቢኖራትም በአግባቡ ጥቅም ላይ ሳይውል ቆይቷል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ዜጎች ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት በማሟላት ኢትዮጵያን የሕክምና ቱሪዝም ማዕከል ማድረግ የሚያስችል ሥራ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መንግስት የዲጂታል የጤና ስርዓት በመዘርጋት በብቁ የሕክምና ባለሙያዎች የተሟሉ የሕክምና ተቋማት እየገነባ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያን የሕክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የሕክምና አገልግሎት መሣሪያዎችና የሕክምና ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ማሳደግ ይገባል ነው ያሉት፡፡ የወራቤ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ካሊድ ሸረፋ፤ ኢትዮጵያን የሕክምና ቱሪዝም መዳረሻ ማድረግ ለሕክምና ወደ ውጭ የሚሄዱ ዜጎችን የሚያውጡትን የውጭ ምንዛሪ ከማስቀረት ባለፈ ለሕክምና ወደ ኢትዮጵያ ከሚመጡ ዜጎች ተጨማሪ ገቢ ማግኘት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ መንግስት የሕክምና ቱሪዝምን ለማሳደግ የሕክምና መሠረተ ልማቶችን እያስፋፋ መሆኑን ገልጸው፤ ጥራት፣ ደህንነትና ተደራሽነትን መሠረት ያደረገ አገልግሎት በመስጠት ሚናቸውን እንደሚወጡም ጠቁመዋል፡፡ የመቅረዝ ጠቅላላ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ናትናኤል ታዬ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያን የሕክምና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የጀመራቸው ሥራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ገልጸው፤ የጤና ተቋማትን ማዘመንና በሀገር ውስጥ የሌሉ ዘመናዊ የሕክምና መሣሪያዎች በስፋት እንዲገቡ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አንስተዋል፡፡ መንግስት የሕክምና መድኃኒቶችና ግብዓቶች በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ለማጠናከር ለፋርማሲዩቲካል ዘርፉ ትኩረት በመስጠት የሕክምና ተቋማት በወቅቱና በዓይነት እንዲደርሳቸው ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አድንቀዋል፡፡
አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ በተሠራው ሥራ የሕክምና ተቋማት አቅምና ዘመናዊነት እያደገ መጥቷል
Jun 15, 2026 595
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤናው ዘርፍ ባከናወናቸው መጠነ-ሰፊ የልማት ሥራዎች የሕክምና ተቋማት አቅምና ዘመናዊነት እያደገ መምጣቱን የከተማዋ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የላፍቶ ሆስፒታልን በቅርቡ በመረቁበት ወቅት፤ የሀገሪቱን የጤና ፖሊሲ ከግምት ውስጥ በማስገባት ኢትዮጵያን ቀዳሚ የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የተሰነቀውን ትልቅ ራዕይ ከግብ ለማድረስ እንደ አንድ ትልቅ የአሸጋጋሪ ምዕራፍ ተጠቃሽ መሆኑን መግለጻቸው ይታወቃል። ይህም ዜጎች ለላቀ የህክምና አገልግሎት ፍለጋ ወደ ውጭ ሀገር በሚጓዙበት ወቅት የሚባክነውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለመቀነስ የሚረዳ ሲሆን፤ የዘርፉን የአገልግሎት ጥራትም ወደ አዲስ ከፍታ ያሸጋግረዋል። ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ያላትን የህክምና ማዕከልነት ሚና ይበልጥ እንደሚያጎላውም መግለጻቸው ይታወሳል። የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ከአዳዲስ ሆስፒታሎች ግንባታ እስከ ዲጂታል የጤና መረጃ ሥርዓት ዝርጋታ የተከናወኑ ተግባራት አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የተያዘው ትልቅ ሀገራዊ ራዕይ አካል ናቸው። በከተማዋ የዘመናዊ ሕክምና አቅምን ከሁለት እጥፍ በላይ ያሳደገ ታሪካዊ ተግባር ተከናውኗል ብለዋል። ባለፉት ዓመታት ዘጠኝ አዳዲስ ዘመናዊ ጤና ጣቢያዎች ወደ አገልግሎት የገቡ ሲሆን፤ በዚህም ከዚህ ቀደም የጤና ተቋም ያልነበራቸውን አምስት ወረዳዎች ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በ40 ነባር የጤና ጣቢያዎች ላይ ሰፊ የማስፋፊያና የማጠናከሪያ ሥራዎች መከናወናቸውንም ነው ያብራሩት። ዘውዲቱ መታሰቢያ፣ ራስ ደስታ ዳምጠው እና ዳግማዊ ምኒሊክን ጨምሮ ነባር ሆስፒታሎች ታድሰዋል፤ አዳዲስ ማስፋፊያ ሕንጻ ተገንብቶላቸዋል ያሉት ኃላፊው፤ የአገልግሎት አቅማቸውም በከፍተኛ ደረጃ እንዲጨምር ተደርጓል ብለዋል። በጤና መሠረተ ልማት ረገድ ከተመዘገቡት ስኬቶች መካከል የአበበች ጎበና እናቶችና ሕጻናት ሆስፒታል ግንባታ በግንባር ቀደምትነት እንደሚጠቀስ ተናግረዋል። አዲስ አበባ የእናቶችና ሕጻናት ሞት ምጣኔን በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ፣ በዘላቂ ልማት ግቦች ሥር የተቀመጠውን ዓለም አቀፍ መለኪያ ካቀደችው ጊዜ አስቀድማ ማሳካቷንም ነው ያነሱት። በከተማዋ የሕክምና ጥራትንና የቴክኖሎጂ አቅምን ዓለም ከደረሰበት ደረጃ የሚያደርሱና ለውስብስብ የሕክምና ዓይነቶች በራስ አቅም አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ልዩ የሕክምና ልህቀት ማዕከላት ወደ ሥራ መግባታቸውን ተናግረዋል። ሁሉም ሆስፒታሎች የራሳቸውን ኦክስጅን በማምረት ቀደም ሲል በሲሊንደር አቅርቦት ላይ የነበረባቸውን ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ አስቀርተዋል ብለዋል። የአገልግሎት ፍጥነትን፣ ወጥነትንና የመረጃ አያያዝን ለማዘመን በተከናወነው ሥራ፤ ጤና ጣቢያዎችን ጨምሮ 67 የጤና ተቋማት በዲጂታል የሕክምና መረጃ ሥርዓት ውስጥ መካተታቸውን ተናግረዋል። በተጨማሪም በመንግስት ድጋፍና ምቹ ሁኔታዎች በመታገዝ የግል ባለሀብቶችም በጤናው ዘርፍ ዘመናዊ ሆስፒታሎችን በማቋቋም ለአገልግሎት ማብቃት መቻላቸውን ገልጸዋል።
የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ በተሳካ ሁኔታ እየተሰጠ ነው-የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
Jun 15, 2026 303
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ በተሳካ ሁኔታ እየተሰጠ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ገለፁ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የሚሰጠው የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዛሬው ዕለት ተጀምሯል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት በከተማ አስተዳደሩ ባሉ 767 ትምህርት ቤቶች የሚገኙ 85 ሺህ 17 የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ። የፈተናውን ሂደት የሚከታተሉ 3 ሺህ 400 የፈተና አስፈጻሚዎች በከተማዋ በሚገኙ በ199 የፈተና ጣቢያዎች መመደባቸውንም ገልጸዋል። ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የሚያስችል ኮማንድ ፖስት መቋቋሙን አንስተው በፈተና ጣቢያዎች አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ ፈተናው መጀመሩን ተናግረዋል። በትምህርት ቤቶች በተደረገው ምልከታ በመፈተኛ ጣቢያዎች ለተማሪዎች በራስ መተማመን የሚፈጥር ዐውድ መኖሩን ተመልክተናል ብለዋል። ተማሪዎች ታዳጊዎች በመሆናቸው በስነልቦና ለማዘጋጀት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። የተማሪዎችን በራስ መተማመን ለማሳደግና ኩረጃን የሚፀየፍ ትውልድ ለመፍጠር የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰራታቸውንም አንስተዋል።
ኢኮኖሚ
የወልዲያ ከተማ የኮሪደር ልማት ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት ከመሆን ባለፈ ምቹ የመዝናኛ ሥፍራ ፈጥሯል
Jun 16, 2026 42
ደሴ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በወልድያ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት ከመሆን ባለፈ ምቹ የመዝናኛ ሥፍራ መፍጠሩን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። በከተማዋ እየተከናወነ ካለው 18 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ 6 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ የሚታወቅ ነው። የኮሪደር ልማቱን በማስመልከት ኢዜአ በወልደያ ከተማ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ የልማት ሥራው ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ከመሆን ባለፈ ምቹ የመዝናኛ ስፍራ ፈጥሮላቸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ጠቅል ንጉሴ የኮሪደር ልማት ሥራው ትውልድን ታሳቢ አድርጎ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ ለልማት ሥራው ውጤታማነት የሚጠበቅባቸውን በመወጣት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማቱ ለወልዲያ ከተማ ተጨማሪ ውበት ከመሆን ባለፈ ለህብረተሰቡ ምቹና አማራጭ የመዝናኛ ስፍራ እየፈጠረ መምጣቱን ገልጸዋል። ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ ታሪኩ ሞገስ በበኩላቸው፣ በሌሎች ከተሞች በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ቁጭት ቢፈጠርባቸውም በአሁኑ ወቅት በከተማዋ በተከናወኑ የልማት ሥራዎች መካሳቸውን ተናግረዋል። "የዘመናት የልማት ጥያቄያችን መልስ አግኝቷል" ያሉት ነዋሪው፣ በተለይ የኮሪደር ልማቱ የወልድያ ከተማን ውበት አጉልቶ ከማውጣት ባለፈ ከተማዋን ለኑሮና ለመዝናኛነት ምቹ ማድረጉን ገልፀዋል። በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ለልማት ሥራ መፋጠን ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸው፣ በቀጣይም የአካባቢያቸውን ሰላም ከማጠናከር ባለፈ ለልማቱ ሲያደርጉት የነበረውን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። በወልዲያ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት ከመሆን ባለፈ ከተማዋ ለቱሪስት፣ ለኢንቨስትመንትና ለኑሮ ምቹ እንድትሆን አድርጓል ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ቸርነት እሸቴ ናቸው። በከተማዋ ቀደም ሲል የነበረው የአስፋልት መንገድ የተበላሸና ጠባብ በመሆኑ ተሽከርካሪ፣ ሰውና እንስሳት እየተጋፉ ሲጓዙ እንደነበር አስታውሰው፣ ይህም ለትራፊክ አደጋ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ብለዋል። የኮሪደር ልማቱ የተሽከርካሪ፣ የብስክሌት እና የእግረኛ መንገድን ከማካተቱ ባለፈ የአረንጓዴ ልማት፣ የመዝናኛ እና የልጆች መጫወቻን ጭምር አካቶ በመከናወኑ ችግሩ መፈታቱን ገልጸዋል። የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው እንዳሉት፣ የከተማውን ሰላም ከማረጋገጥ ባለፈ ህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። በከተማው 18 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንና ከዚህ ውስጥ 6 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትሩ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉን አመልክተዋል። ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው የኮሪደር ልማት ከስታድየም-ጎንደር በር፤ ከጎንደር በር- ሙጋድ፤ ከአዳጎ አደባባይ-ሙጋድ፤ ከአዳጎ አደባባይ -ፒያሳ እና - መነኸሪያ የተከናወኑ ልማቶችን ያካተተ እንደሆንም አስረድተዋል። ቀሪውን የኮሪደር ልማት ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ህብረተሰቡን ባሳተፈ አግባብ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ዱባለ ተናግረዋል።
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሐቆች
Jun 16, 2026 277
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስጀምረውታል። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ከባሕር ጠለል በላይ በ1 ሺህ 910 ሜትር ከፍታ ላይ እየተገነባ ይገኛል። በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ ዐቅም አለው። አሁን ካለው የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የማስተናገድ ዐቅም ጋር ሲነጻጸር በ4 ነጥብ 4 እጥፍ ብልጫ ይኖረዋል። ይህ ታሪካዊ ፕሮጀክት፣ ሀገራችንን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ማዕከላት ተርታ ለማሰለፍ ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ጥረት እየተገነባ ይገኛል። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት ነው። የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታው የሚከናወነው በሁለት ምዕራፍ ነው። የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ 60 ሚሊየን መንገደኞች የማስተናገድ ዐቅም በመያዝ እንደ አውሮውፓውያን አቆጣጠር በ2030 እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል። በዚህ ምዕራፍ አንድ እጅግ ትልቅና ዘመናዊ እንዲሁም አንድ መለስተኛ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናሎች ይገነባሉ። በተጨማሪም በመጀመሪያው ምዕራፍ ሁለት በተጓዳኝ የሚሠሩ የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች እንዲሁም 180 አውሮፕላኖችን በአንድ ጊዜ ማቆም የሚያስችል ቦታ ይገነባል። በዚሁ ምዕራፍ 350 ማረፊያ ክፍሎች ያሉት ዘመናዊ ሆቴል በተርሚናሉ ውስጥ ይገነባል። በዓመት 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን ጭነት የሚያስተናግድ የካርጎ ተርሚናል እና የአውሮፕላን ጥገና ማዕከልም በዚሁ ምዕራፍ የሚገነባ ይሆናል። ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ አህጉርም ትልቅ አርአያ ነው። የአፍሪካ ነፃ አኅጉራዊ ንግድ ቀጣናን ተግባራዊነት ለማቀላጠፍና የአኅጉሪቱን የንግድና የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር ቁልፍ ሚና ይጫወታል። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር የሚያገናኝና በአንድ ጊዜ 12 ተሽከርካሪ ማስተናገድ የሚችል የፍጥነት መንገድ እንዲሁም ፈጣን የባቡር መንገድ ይገነባል። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የአፍሪካን አቪዬሽን እድገት አስሮ የያዘውን የመሠረተ-ልማት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው። ይህ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት ከፍተኛ የሥራ ዕድል ይፈጥራል። ከአውሮፕላን ማረፊያው ጋር ተያይዞ የሚመሠረተው የኤርፖርት ከተማም በንግድ፣ በኢንዱስትሪና በቱሪዝም ዘርፎች ለአካባቢው ዕድገት ትልቅ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።
ረቂቅ አዋጁ ዘመናዊ የታክስ ሥርዓት ለመዘርጋት ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል - ቋሚ ኮሚቴው
Jun 15, 2026 471
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ዘመናዊ የታክስ ሥርዓት ለመዘርጋት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ የሕዝብ ይፋዊ ውይይት መድረክ አካሂዷል። በገንዘብ ሚኒስቴር የሕግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ተወዳጅ መሀመድ የማሻሻያ አዋጁን መነሻ ሃሳብ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት አዋጁ የታክስ አስተዳደሩን ቀልጣፋ በማድረግ የሀገርን ኢኮኖሚ ማሳደግ የሚያስችል ነው። የግብር ከፋዮችን መብትና ግዴታ ሚዛናዊ በሆነ መልኩ በማስከበር ፍትሐዊነትንና ታክስ የመክፈል ግዴታን በተጠናከረ መልኩ ማስፈፀም እንደሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም ታክስ ከፋዩ በታክስ ሥርዓቱ አመኔታ ኖሮት ግዴታውን በአግባቡ እንዲወጣ እንደሚረዳ ገልፀዋል። የገቢዎች ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ወሀብረቢ የታክስ አስተዳደር አዋጁ ማሻሻያ የተቀላጠፈ ሥርዓት በመገንባት ከግብር ከፋዩ የሚነሱ ቅሬታዎችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል እንደሆነ አስታውቀዋል። ታክስን በአግባቡ በመሰብሰብ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያስፈልገውን ፋይናንስ በውስጥ አቅም መሸፈን የሚያስችል ሁኔታ የሚፈጥር ነው ብለዋል። ከሰው ንክኪ ነፃ የሆነ በዲጂታል የተደገፈ አሠራር በመዘርጋት ተደራሽነትና ቅልጥፍናን በማረጋገጥ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ከብልሹ አሠራር ነፃ እንዲሆን ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጆ በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ በታክስ ሥርዓቱ ላይ ተግዳሮት የሆኑ ጉዳዮችን ለማረም መዘጋጀቱን አንስተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰበሰበው የታክስ ገቢ እያደገ ነው ያሉት ሰብሳቢው ይህም የማክሮ ኢኮኖሚ፣ የፊሲካል ፖሊሲና የታክስ ሥርዓት ማሻሻያዎችን ውጤታማነት የሚያሳይ መሆኑን ገልፀዋል። በግብር ከፋዩ ዘንድ እየተሠራ ያለው የግንዛቤ ፈጠራ እና ማበረታቻ የግብር ከፋዮችን ተነሳሽነት በማሳደግ ግዴታቸውን እንዲወጡ እያስቻለ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር 11 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በደን መሸፈን አስችሏል
Jun 15, 2026 565
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር 11 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በደን እንዲሸፈን ማስቻሉን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ዛሬ በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ በይፋ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት በዚህ ዓመት 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ በማስቀመጥ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊየን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን ብለዋል። የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ እንዳሉት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መንግሥትና ሕዝብ ተቀናጅተው ያሳኩት ታላቅ ታሪክ ነው። ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት ሰባት ዓመታት 48 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸውን አንስተው በየዓመቱ በአማካይ 25 ሚሊየን ዜጎች በመርሃ ግብሩ መሳተፋቸውንም ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ከተተከሉት ችግኞች መካከል 60 በመቶ ያህሉ ለጥምር እርሻ የሚውሉ መሆናቸውን አንስተው 35 በመቶ ያህሉ ደግሞ የደን ዛፎች ናቸው ብለዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ትግበራ 11 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በደን እንዲሸፈን ማስቻሉንም አስረድተዋል። የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደጉ ባለፈ የአረንጓዴነት ምጣኔን በመጨመር ወደ ውሃ አካላት የሚወርደውን የደለል መጠን እንዲቀንስ አስችሏል ነው ያሉት። የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ በየዓመቱ ወደ ወንዞች ታጥቦ ይገባ የነበረውን የአፈር ሀብት ከ2 ቢሊየን ቶን ወደ 208 ሚሊየን ቶን ዝቅ እንዲል ማስቻሉን ተናግረዋል። መርሃ ግብሩ የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነትን ማሳደግ ማስቻሉን አንስተው የመድረቅ አደጋ ተጋርጦባቸው የነበሩ የውሃ አካላት እንዲያገግሙ አድርጓልም ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መቋቋም የሚያስችል አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባትም ትልቅ አቅም እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በአዲስ አበባ ከታቀደው በላይ ዜጎች የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠናን ለመውሰድ ተመዝግበዋል
Jun 16, 2026 20
አዲስ አበባ፤ሰኔ 9/2018(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በእቅድ ከተያዘው በላይ ዜጎች የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠናን ለመውሰድ መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታወቀ። በከተማዋ ከ809 ሺህ በላይ ዜጎች የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠናን እንዲወስዱ ለማድረግ ታቅዶ፥ ከ996 ሺህ በላይ ዜጎች ስልጠናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን ቢሮው ገልጿል። እስካሁን ባለው ሂደት ስልጠናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት ዜጎች መካከል ከ742 ሺህ የሚሆኑትም ስልጠናውን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት ወስደዋል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ምህዳር ውስጥ ንቁ ተሳታፊና ተወዳዳሪ ለመሆን በዲጂታል መሠረተ ልማትና በዲጂታል ክህሎት እየተዘጋጀች ነው። የዚህ ብሔራዊ ግብ አካል የሆነው የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ መርሃ ግብር ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ መጀመሩ ይታወሳል። በሦስት ዓመት ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ 5 ሚሊዮን ወጣቶች በኦንላይን የኮዲንግ ስልጠና እንዲወስዱ ዓላማ ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ ባስተላለፉት መልዕክት በመርሃ ግብሩ በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ስልጠናውን ማጠናቀቃቸውንና ይህ ስኬት የሕዝቡ ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የስማርት ሲቲ ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ቱሉ ጥላሁን ለኢዜአ እንዳሉት፥ የ5 ሚሊዮን ኮደሮች መርሃ ግብር የዲጂታል ክህሎትን የሚያሳድግ ነው። የኮደርስ ስልጠናዎች የዲጂታል ክህሎትን ከማሳደጋቸው በተጨማሪ የፈጠራ ሃሳብን የሚያጎለብቱና ቴክኖሎጂ ለማልማት የሚችሉበት እድል የሚፈጥር መሆኑንም ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ከ800 ሺህ በላይ የሰው ኃይልን ለማሰልጠን መታቀዱንና ጠቅሰው፥እስካሁን ባለው መረጃ ከ90 በመቶ በላይ ያህል ዜጎች ስልጠናቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልፀዋል። በከተማዋ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ እቅድን ለማሳካት ቢሮው ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑንም አንስተዋል። ቢሮው የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት የሚያጠናክሩ ሌሎች ዘመናዊ ስርዓቶችን ወደተግባር በማስገባት ስልጠና ለመስጠት ማቀዱን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የኮደርስ ሰልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ መታቀዱንና ይህንን ብሔራዊ ተልዕኮ ለማሳካትም ዜጎች በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቀን ከ250 ሲሊንደር በላይ የሕክምና ኦክስጅን በማምረት ከራሱ አልፎ ለአካባቢ የህክምና ተቋማት ማቅረብ ጀምሯል
Jun 16, 2026 130
አዲስ አበባ፤ሰኔ 9/2018(ኢዜአ)፦የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቀን ከ250 ሲሊንደር በላይ የሕክምና ኦክስጅን በማምረት ከራሱ አልፎ ለአካባቢ የህክምና ተቋማት ማቅረብ መጀመሩን ገለጸ፡፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመትና የማስተማሪያ ሆስፒታሉን 100ኛ ዓመት ባለፈው ዓመት ማክበሩ ይታወሳል፡፡ በዚህም ዩኒቨርሲቲው የተቋቋመበትን የማህበረሰቡን ችግር ፈች አገልግሎት የመስጠት ዓላማ ታሳቢ በማድረግ ከ20 በላይ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል፡፡ የጨረር ሕክምና ማዕከል፣ የሕክምና ኦክስጅን ማምረቻ፣ ዘመናዊ የደረቅና እርጥብ ቆሻሻ ማስወገጃና ሌሎችም ማህበረሰብ አቀፍ ፕሮጀክቶች በምርምር ተቋቁመው ገቢራዊ ተደርገዋል፡፡ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የምህንድሥና ሥራ አገልግሎት ዳይሬክተር እና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢንጂነር ወንደወሰን በየነ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል ታካሚዎች ሕክምና የሚያገኙት ከአዲስ አበባ ተገዝቶ በሚመጣ የሕክምና ኦክስጅን ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት ማዕከሉ በቀን 250 ሲሊንደር እና ለ600 የህሙማን አልጋዎች በቀጥታ የሚደርስ የሕክምና ኦክስጅን በማምረት እጥረቱን ሙሉ በሙሉ መፍታት ችሏል ብለዋል፡፡ የሕክምና ኦክስጅን ማዕከሉ ኦክስጅን ለማምረትየተፈጥሮን አየርን በማጣራት ጥቅም ላይ እንደሚያውል ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከራሱ አልፎ ለአካባቢው የሕክምና ተቋማት የሕክምና ኦክስጅን እያቀረበ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ አድማሱን በማስፋት ምርቱን የማሳደግና ገቢ የማመንጨት እቅድ ይዟል ብለዋል፡፡
የጅማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የስራ ተነሳሽነትን አሳድጓል
Jun 15, 2026 416
ጅማ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሚገኙ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት፣ ለማህበረሰቡ እየሰጡት ካለው ቀልጣፋና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በተጨማሪ የአገልጋዮችን የስራ ተነሳሽነት ማሳደጋቸው ተገለጸ። ማዕከላቱ በብቁ ባለሙያዎች መደራጀታቸውና ዘመናዊ አሰራርን መከተላቸው ለአገልጋዩም ሆነ ለተገልጋዩ ትልቅ እረፍት መሆኑ ተመላክቷል። የሊሙ ገነት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባለሙያዎች ሪዳ ከማል እና አዳል ኃይለማርያም፤ በማዕከሉ ለህብረተሰቡ የሚሰጡት አገልግሎት የስራ ተነሳሽነት እንደጨመረላቸው ገልጸዋል። ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የተደራጀ በመሆኑ የአገልግሎት ፍጥነቱን ከመጨመሩ በላይ የሰራተኛውንም ሆነ የህብረተሰቡን ውድ ጊዜ መቆጠብ አስችሏል። በተመሳሳይም የጅማ ማዕከል ባለሙያዎች አብዱልኑራ አባተማም እና ሰሚራ ሐሰን በበኩላቸው፣ ምቹ የስራ ቦታ መፈጠሩ ያለምንም የተገልጋይ ቅሬታ ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። ሌላው በዞኑ በቅርቡ አገልግሎት በጀመረው የኦሞ ናዳ ወረዳ አሰንዳቦ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል በማገልገል ላይ የሚገኙት ማረሜ በቀለ እና አንዋር አባዲጋ፣ ለማህበረሰቡ በንቃትና በትጋት አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ምቹ የስራ ሁኔታ መኖሩ ሰራተኞች ያለመሰልቸት በቁርጠኝነት እንዲሰሩ ማድረጉን የጠቀሱት ባለሙያዎቹ፣ በዚህም ለዓመታት የህብረተሰቡ የቆየ ጥያቄ የነበረው የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ሙሉ በሙሉ መቀረፉን አስታውቀዋል። በማዕከላቱ አገልግሎት ለማግኘት የመጡት ሙስጠፋ አብዱረህማን በበኩላቸው፣ በአካባቢያቸው እንዲህ ያለ ዘመናዊ ማዕከል መከፈቱ በእጅጉ እንዳስደሰታቸው ገልጸው፤ ገና ወደ ማዕከሉ ስገባ ከመስተንግዶው ጀምሮ የባለሙያዎቹ አቀባበልና ፍጥነት ከፍተኛ እርካታ የሚሰጥ ነው ብለዋል። ለመንጃ ፈቃድ አገልግሎት የመጣው ጀማል አብዱረህማንም ማዕከሉ ከምንም በላይ ወደ ህብረተሰቡ የቀረበና ለዓመታት ለነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠ መሆኑን ተናግሯል። በጅማ ከተማ በሚገኘው ማዕከል የልደት ካርድ ለማውጣት የመጣችው የጅማ ከተማ ነዋሪ ቤተመቅደስ አምሀ፣ ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል ማግኘቷ እንዳስደሰታት ገልጻለች። የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምክትል ሥራ አስኪያጅ እና የቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ ጀማል ሳሊ፣ በማዕከሉ የሚሰጠው አገልግሎት ለተገልጋዩ ብቻ ሳይሆን ለአገልጋዮችም ጭምር የእርካታ ምንጭ መሆኑን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ ጊዜና ገንዘቡን ቆጥቦ ፈጣን አገልግሎት አግኝቶ መመለሱና በተሰጠው አገልግሎት ረክቶ የሚሰጠው አዎንታዊ ምላሽ ለሰራተኛው ትልቅ ተነሳሽነት መፍጠሩን አብራርተዋል።
"ቤጉ መሶብ" አዳዲስ አገልግሎቶችን በማካተት ተደራሽነቱን እያሰፋ ነው
Jun 15, 2026 328
አሶሳ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ (ቤጉ) መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አዳዲስ አገልግሎቶችን በውስጡ በማካተት ለተገልጋዮች ያለውን ተደራሽነት እያሰፋ መሆኑ ተገለጸ። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እያደገ የመጣውን የንግድ፣ የግብርና እና የኢንቨስትመንት ፍላጎት ለማስተናገድ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን ለማዘመን በትኩረት እየሰራ ይገኛል። በዚህም ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ በአምስት የክልል እና ሶስት የፌደራል ተቋማት 33 አገልግሎቶችን አካቶ ስራ የጀመረው "ቤጉ መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአሁኑ ሰዓት አገልግሎቱን በማስፋት ተደራሽነቱን እያሳደገ ይገኛል። የቤጉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ኢንጂነር ሰመረ ጅራታ እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ በአሁኑ ሰዓት 33 የነበሩትን አገልግሎቶች ወደ 42 በማሳደግ ዜጎች ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ለማድረግ እየሰራ ነው። ፍትህ ቢሮ እና የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በማዕከሉ እየሰጧቸው ከሚገኙ አገልግሎቶች በተጨማሪ ውልን መርምሮ ማጽደቅ እና የመድን ፈንድ አገልግሎት መስጠትን የመሳሰሉ አዳዲስ የስራ ዘርፎችን በማካተት የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በቅርቡም የክልሉ ማዕድን ቢሮን ጨምሮ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና ሌሎች ተቋማት ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል። ቤጉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እስካሁን ድረስ ከ28 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠቱን ጠቁመው፤ የተገልጋዮች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል። ቤጉ መሶብ በቅርቡ ስራ ለጀመረው አሶሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም አስፈላጊውን የሙያ ዕገዛ በማድረግ ማዕከሉ በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገባ ማድረጉን አብራርተዋል። በቅርቡም በባምባሲ፣ ግልገል በለስ እና ካማሽ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።
ስፖርት
አርጀንቲና ከአልጄሪያ፣ ፈረንሳይ ከሴኔጋል – የዓለም ዋንጫው ወሳኝ ፍልሚያዎች
Jun 16, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የስድስተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በምድብ 10 የወቅቱ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ አርጀንቲና ከአልጄሪያ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በካንሳስ ሲቲ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል። ሁለቱ ቡድኖች በዓለም ዋንጫ መድረክ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም እ.አ.አ በ2007 ባደረጉት ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታ አርጀንቲና 4 ለ 3 አሸንፋለች። ለ19ኛ ጊዜ በዓለም ዋንጫው ተሳትፎ የምታደርገው አርጀንቲና የሶስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ናት። የወቅቱ የዋንጫ ባለቤትም ናት። የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጄሪያ በዓለም ዋንጫው ስትሳተፍ የአሁኑ ለአምስተኛ ጊዜ ነው። አልጄሪያ እ.አ.አ በ2014 በብራዚል በተካሄደው 20ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ደርሳ በጀርመን 2 ለ 1 ተሸንፋ ከውድድሩ የተሰናበተችበት አጋጣሚ በውድድሩ ታሪክ ትልቁ ውጤቷ ነው። የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ያነሳሉ ተብለው ከሚጠበቁት ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው አርጀንቲና ጨዋታውን የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት አግኝታለች። ተጋጣሚዋ አልጄሪያው በጨዋታው ላይ በቀላሉ እጅ ትሰጣለች ተብሎ አይጠበቅም። በምድብ ዘጠኝ ፈረንሳይ ከሴኔጋል ምሽት አራት ሰዓት በሜት ላይፍ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። እ.አ.አ በ2002 ጃፓን እና ኮሪያ ሪፐብሊክ በጣምራ ባዘጋጁት 17ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ላይ ቡድኖቹ ያደጉት ጨዋታ አይረሴ የታሪክ ክስተት የተስተናገደበት ነበር። እ.አ.አ በ1998 16ኛውን የዓለም ዋንጫ ራሷ አዘጋጅታ ሀገሯ ላይ ዋንጫውን ያስቀረችው ፈረንሳይ ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ ግምት ተሰጥቷታል። በሴኡል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሴኔጋል በፓፓ ቡባ ዲዮፕ የ30ኛ ደቂቃ ጎል ፈረንሳይን 1 ለ 0 በማሸነፍ ዓለምን ጉድ ያስባለ ድል አስመዘገበች። ሴኔጋል በወቅቱ እስከ ሩብ ፍጻሜ የደረሰች ሲሆን ፈረንሳይ ከምድቡ ማለፍ አለመቻሏ በወቅቱ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። ከዚህ ክስተት 24 ዓመታት ቆይታ በኋላ ሀገራቱ በድጋሚ የሚገናኙበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ፈረንሳይ በዓለም ዋንጫው ለ16ተኛ ጊዜ የምትሳተፍ ሲሆን ሁለት ጊዜ ዋንጫውን አንስታለች። በውድድሩ ላይ ለአራተኛ ጊዜ ተሳትፎዋን የምታደርገው ሴኔጋል ትልቁ ውጤቷ በ17ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ የደረሰችበት ነው። በሌሎች መርሐ ግብሮች በምድብ 10 ኦስትሪያ ከጆርዳን ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በሳንፍራንሲስኮ ቤይ ስታዲየም ይጫወታሉ። በምድብ ዘጠኝ ኢራቅ ከኖርዌይ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በቦስተን ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 35ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል
Jun 16, 2026 159
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ35ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። የዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና መቀሌ 70 እንደርታን ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ያገናኛል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ46 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በ35 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ኢትዮ ኤሌክትሪክ የአሸናፊነትን መንገድ ለማግኘት ይጫወታል። ካለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች በአንዱ ብቻ ሶስት ነጥብ ያገኘው መቀሌ 70 እንደርታ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት በሚያደርገው ትግል የዛሬውን መርሐ ግብር በድል መወጣት ይኖርበታል። በሌላኛው መርሐ ግብር ባህር ዳር ከተማ ከወላይታ ድቻ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች አቻ የተለያየው ባህር ዳር ከተማ በ46 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። ባህር ዳር ከተማ በውድድር ዓመቱ በርካታ ጨዋታዎች አቻ የወጣ (19 ጊዜ) ቡድን ነው። ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች አቻ የተለያየው ወላይታ ድቻ በ44 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ወላይታ ድቻ ከባህር ዳር ከተማ በመቀጠል በሊጉ በርካታ ጨዋታዎች አቻ የተለያየ (17 ጊዜ) ቡድን ነው። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ሸገር ከተማ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። በ34ኛ ሳምንት ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 የረታው ሸገር ከተማ በ43 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ተጋጣሚው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ በ41 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። ጨዋታው ሸገር ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።
ኢራን ከኒውዝላንድ ሳዑዲ አረቢያ ከኡራጓይ ያደረጓቸው ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ
Jun 16, 2026 126
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል። በሎስ አንጀለስ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ ሰባት ጨዋታ ኢራን እና ኒውዝላንድ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ራሚን ሬዛን እና መሐመድ ሞሄቢ ለኢራን ግቦቹን አስቆጥረዋል። ኤሊጃህ ጀስት የኒውዝላንድን ግቦች አስቆጥሯል። ኢራን በጨዋታው ላይ ሁለት ጊዜ ተመርታ የአቻ ውጤት ማስመዝገብ ችላለች። በዚሁ ምድብ ትናንት ማምሻውን ቤልጂየም እና ግብጽ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ኒውዝላንድ ከግብጽ፣ ቤልጂየም ከኢራን ቀጣይ የሚደረጉ የምድብ ሰባት ጨዋታዎች ናቸው። በተያያዘም በሚያሚ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ ስምንት ሁለተኛ ጨዋታ ሳዑዲ አረቢያ እና ኡራጓይ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። አብዱሌላህ ኤል-አምሪ ለሳዑዲ አረቢያ፣ ማክሲ አራውጆ ለኡራጓይ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በዚሁ ምድብ ትናንት በተደረገው ጨዋታ ኬፕቨርዴ ከስፔን ጋር ያለ ግብ አቻ በመውጣት ያገኘችው ውጤት ያልተጠበቀ ሆኗል። በምድብ ስምንት ሁለተኛ መርሐ ግብር ኡራጓይ ከኬፕቨርዴ፣ ስፔን ከሳዑዲ አረቢያ ይጫወታሉ።
ቤልጂየም እና ግብጽ ነጥብ ተጋርተዋል
Jun 16, 2026 117
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የምድብ ሰባት መርሐ ግብር ቤልጂየም እና ግብጽ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ትናንት ማምሻውን በሲያትል ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢማም አሹር በ20ኛው ደቂቃ ግብጽን መሪ ያደረገችውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። የግብጹ መሐመድ ሀኒ በ66ኛው ደቂቃ በራሱ ላይ ያስቆጠረው ጎል ቤልጂየምን አቻ አድርጓል። በጨዋታ ቤልጂየም የተሻለ የኳስ ቁጥጥር ቢኖራትም ግብጽ የግብ እድሎችን በመፍጠር ብልጫ ወስዳለች። ውጤቱን ተከትሎ ሀገራቱ በዓለም ዋንጫው የመጀመሪያው ነጥባቸውን አግኝተዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በባሌ ዞን ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እየተደረገ ነው
Jun 16, 2026 77
ሮቤ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል። ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ሥራ ላይ በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥሪ ማቅረባቸውም ይታወሳል። በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ስኬታማ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ሥራ እየተሠራ ይገኛል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሙአዊያ ፉአድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ባለፉት ዓመታት ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በተከናወነው መርሃ ግብር የተራቆተ መሬትን መልሶ በደን በመሸፈን ረገድ ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል። ይህንን ተግባር ለማስቀጠልም በመጪው ክረምት የሚተከሉ ከ229 ሚሊዮን የሚበልጡ ችግኞችን በመንግስት፣ በማህበራትና በግል የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች የማዘጋጀቱ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። እስካሁን ከ211 ሚሊዮን በላይ ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን፣ 194 ሚሊዮን የሚሆኑ የመትከያ ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውንና ቀሪው ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በዞኑ በችግኝ ማፍያ ጣቢያዎቹ በአብዛኛው ሀገር በቀልና ሌሎች የውጭ ዝርያ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በጽህፈት ቤቱ የተፋሰስና የደን ልማት ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ ኦሊቃ ናቸው። አካባቢው በዓመት ሁለት ጊዜ የበልግና የክረምት ዝናብ የሚያገኝ በመሆኑ ተከላውም ይህንን ስነ-ምህዳር ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ከመጋቢት መጀመሪያ እስከ ሚያዝያ መጨረሻ በጣለው የበልግ ዝናብ 105 ሚሊዮን የሚሆኑ ችግኞች መተከላቸውንና ቀሪው ተከላ በሐምሌ ወር እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል ጥድ፣ ኮሶ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ፣ ግራቪሊያ፣ የእንስሳት መኖና የጥላ ዛፎች የሚገኙበት ሲሆን፣ 8 በመቶ ያህሉ ደግሞ ለሰው ምግብነት የሚውሉ አትክልትና ፍራፍሬ ናቸው ብለዋል። የሐረና ቡሉቅ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ሐሰን፤ በወረዳው የህዝቡን የድርቅ ተጋላጭነት ለመከላከል የተጀመረው ጥረት ህብረተሰቡን በማሳተፍ መጠናከሩን ገልጸዋል። በዚህም በ60 በመቶው የበልግ ዝናብ በመጠቀም፣ ለተከላ ከተዘጋጁ 25 ሚሊዮን ችግኞች መካከል ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውን መትከል መቻሉን አስታውቀዋል። ከወረዳው ነዋሪዎች መካከል አርብቶ አደር ጀማል ሁሴን በሰጡት አስተያየት፤ የድርቅ ተጋላጭነትን ለመቀነስ ችግኝ መትከል የህልውና ጉዳይ መሆኑን ካለፉት ዓመታት ተጨባጭ ውጤት መረዳታቸውንና በዘንድሮው መርሃ ግብር ላይ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። በባሌ ዞን ባለፈው የክረምት ወቅት ከተተከሉ ከ245 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መካከል በተደረገ ቆጠራ 87 በመቶው ጸድቆ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለከተማዋ አካባቢ ጥበቃ፣ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 16, 2026 146
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአጋሮ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ፣ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የከተማዋ አስተዳደር ገለጸ። የከተማዋ ወጣቶችም በአረንጓዴ አሻራ ሥራ ላይ በማህበር ተደራጅተው በመስራታቸው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ከማሳደጋቸው ባለፈ ለሌሎች ሰዎችም የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን በማፍላትና በመትከል እንዲሁም በመንከባከብ የጽድቀት መጠናቸውን በማሳደግ ካላቸው ሁሉ አቀፍ ጥቅም በተጨማሪ ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፉ ማድረግ ይጠበቃል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ልክ እንዳለፉት ጊዜያት ሁሉ ዘንድሮም በችግኝ ተከላው ተሳትፎውን በማጠናከር አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ዘላቂ ሕይወት ያለው አካባቢ ለመፍጠር መሥራት ይገባዋል። የአጋሮ ከተማ ነዋሪዎች ቀደም ባሉት ጊዜያት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ ተከላ ሥራው ላይ በንቃት በመሳተፋቸው ተጠቃሚነታቸው ማደጉ ተመላክቷል። ዘንድሮ በሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይም በንቃት እና በተደራጀ አግባብ በመሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰሩ ተገልጿል። የአጋሮ ከተማ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እንዳለ ማመጫ እንደገለጹት፣ በከተማዋ ባለፉት ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ገብር ላይ ህብረተሰቡን በስፋት በማሳተፍ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል። በዚህም ለከተማዋ አካባቢ ጥበቃ፣ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ሲሉም ገልጸዋል። በዚህም ህብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ መሆኑ በተጨባጭ መታየቱን ጨምረው ተናግረዋል። በዘር ዝግጅት፣ ችግኝ በማፍላት፣ በመጓጓዣ፣ በተከላ፣ በደን እንክብካቤ እና በአካባቢ ጥበቃ ዘርፎች ላይ ለበርካታ ሰዎች የአጭርና የረጅም ጊዜ የሥራ ዕድሎች መፍጠር መቻሉንም አክለዋል። ዘንድሮ ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ የተለያዩ ዝርያዎች ያላቸው ችግኞች ዝግጅት መከናወኑንም ጠቁመዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አረንጓዴ ኢኮኖሚን ከመገንባትና አካባቢን ከማስዋብ ባሻገር የሥራ ዕድል በመፍጠር የህብረተሰቡን ኑሮ ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እንዳለውም በሥራው ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል። በዘርፉ ተሰማርተው ውጤታማ ከሆኑ ወጣቶች መካከል ፈሪድ ነዚፍ እንደተናገረው፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በማህበር ተደራጅተን በመስራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችን ከማደጉ ባለፈ ለሌሎች ሰዎችም የሥራ ዕድል መፍጠር ችለናል ብሏል። ወጣት ኑሬ አባ ጀባል በበኩሉ፣ በማህበር ተደራጅተው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሚሰሩት የ"grafting" (የተክል ማጣመር) ሥራን በመሥራትና በመሸጥ ቤተሰባችንን እያስተዳደርን እንገኛለን ሲል ገልጿል። ሌላኛው ወጣት ምርጋኒ አባ ፊጣ በበኩሉ፣ በማህበር ተደራጅተን በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞች ዝግጅት ላይ በመሳተፍ ተጠቃሚነታችን እያደገ ነው ብሏል። በአረንጓዴ አሻራ ዘርፍ ላይ በምንሰራው ስራ ሁሉ የከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ አልተለየንም ያለው ወጣት ምርጋኒ ለወጣቶችና ለሴቶች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ገቢያቸው እንዲሻሻል እያደረገ ይገኛል ሲል ተናግሯል።
አረንጓዴ ዐሻራ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልፅግና አሰናስሎ የሚያረጋግጥ ወሳኝ የልማት አቅጣጫ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jun 15, 2026 825
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልፅግና አሰናስሎ የሚያረጋግጥ ብሔራዊ የልማት አቅጣጫ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ ኮፕ-32ን ስታስተናግድ 65 ቢሊየን ችግኞችን መትከል የቻለች ሀገር መሆኗን ለዓለም እናበስራለንም ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ አስጀምረዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የዘንድሮው አረንጓዴ ዐሻራ ማስጀመሪያ በቢሾፍቱ ከተማ መካሄዱ ከተማዋ ከራሷ አልፎ ለአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ችግኞችን የምታመርት መሆኗን ዕውቅና የሚሰጥ ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልፅግና አሰናስሎ የሚያረጋግጥ ብሔራዊ ኢኒሼቲቭ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የደን፣ የሰብልና ሁለንተናዊ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ወሳኝ የልማት አቅጣጫ መሆኑን አስረድተዋል። የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት የሚደፈረው በሁለት ጉዳዮች ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አንዱ ባዕዳን ኃይሎች አልመውና ድንበር ጥሰው ሲገቡ ሲሆን፤ ሌላኛው የእኛ ሃብትና ንብረት በዋዛና ፈዛዛ ሲወጣም የሉዓላዊነት መደፈር ነው ብለዋል። ኢትዮጵያም ባለፉት ዓመታት ያጣችው የአፈር መጠን በገንዘብ ሊተመን የማይችል ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ገልጸዋል። የእኛ አባቶች ዓድዋ ላይ ወራሪን በማሳፈር ገድል ሠርተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የእኛ ትውልድም በአረንጓዴ ዐሻራ ሌላኛውን ለትውልድ የሚሻገር ታላቅ ገድል እየሰራ ነው ብለዋል። የዘንድሮው "ተስፋን እንትከል" መሪ ሃሳብ የነገን ብሩህ ዛሬ በመፃፍ፣ የተስፋ ስሮች ዘልቀው የብልፅግና ግንድ፣ ቅርንጫፍና ፍሬ ተስፋፍቶ ሃብት እንዲሆኑ የሚያመላክት መሆኑንም ተናግረዋል። የተስፋ ምርጫም የቢሾፍቱ ከተማ ነዋሪዎችና መላው ኢትዮጵያውያን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የትኛውም የአየር ሁኔታ ሳይበግራቸው ተስፋን በመሰነቅ ድምፅ መስጠታቸውን ከመሪ ሃሳቡ ጋር አሰናስለው አስገንዝበዋል። ተስፋ የአረንጓዴ መቀነት ነው፣ ሀገርን ያለብሳል፣ የተራቆተና የገረጣን መሬትም ያለመልማል፣ ተስፋ አረንጓዴ ፀዳልና መንፈስን የሚያድስ አረንጓዴ ወርቅ ነው ብለዋል። በተጨማሪም የአረንጓዴ ውርስ ትውልድ የሚከበርበት ቀጣዩ ትውልድ ልምድና ባህል የሚያደርገው የብልፅግና መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ በመደመር መርህ የኢትዮጵያን የተረጂነት ታሪክ ወደ ማድረግ ዘመን የሚያሸጋግር መሆኑን አንስተው፤ መርሃ ግብሩ አፈራችንን ከስደት፥ ግድባችንን ከደለል የሚታደግ ስኬታማ የልማት ዓምድ ነው ብለዋል። ከአስር በላይ አዳዲስ የፍራፍሬ ዝርያዎችን በኢትዮጵያ በማላመድ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለዚህ ስኬትም ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ በችግኝ ማፍላት፣ በእንክብካቤ፣ በመትከል፣ በችግኝ ሽያጭ፣ በንብ ማነብና በእንስሳት ማድለብ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል። በቀጣይም የበለፀገች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ በሁሉም መስክ የተመዘገበውን ስኬት ማስፋትና ማስቀጠል እንደሚያስፈልግም አፅንኦት ሰጥተዋል። ከ2011 ዓም ጀምሮ በተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ48 ቢሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ጠቁመው፥ ዘንድሮም ከስምንት ቢሊየን በላይ ችግኝ በመትከል በአጠቃላይ 56 ቢሊየን እንደሚደርስ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ-32ን ስታስተናግድ 65 ቢሊየን ችግኞችን መትከል የቻለች ሀገር መሆኗን ለዓለም እናበስራለን ብለዋል። ለዚህም ሁሉም ዜጋ የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬት በማስቀጠል በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል። በሚቀጥሉት የክረምት ወራትም "ተስፋን በመትከል" በዓድዋ ድል ቅድመ አያቶች የተቀዳጁትን ድል በአረንጓዴ አሻራ ልማት በመድገም የኩራት ምንጭ የሆነች ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ ብሔራዊ ሥራችን ከተፈጥሮ የመታረቅ በልማት የመላቅ አዲስ ጎዳና ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 15, 2026 623
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ ብሔራዊ ሥራችን ከተፈጥሮ የመታረቅ በልማት የመላቅ አዲስ ጎዳና ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት ለአንዲት ኢትዮጵያ እንደ አንድ ሕዝብ ተደምረን በሠራነው የአረንጓዴ ዐሻራችን፣ ልምላሜ የተራቡ ተራሮች አረንጓዴ ለብሰዋል ብለዋል። ምንጮች እና ተፋሰሶች ምድሩን አረስርሰዋል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በረሃማነት ይጸናባቸው የነበሩ ክበበ ምድሮች ነፋሻማ ሆነዋል ሲሉም ገልጸዋል። የተፈጥሮን ጫና ተቋቁመናል! ይህ ደግ የተፈጥሮ ዕርቅ ነው ሲሉም ተናግረዋል በመልዕክታቸው። የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥን ከተፈጥሮ ጥበቃ ጋር በማስተሣሠር በተሠራው ሥራ የፍራፍሬ ተክሎች በስፋት ለምተዋል፤ ፍሬ መስጠትም ጀምረዋል ብለዋል። ይህም በምግብ ራስን ለመቻል ለጀመርነው ብሔራዊ ኢኒሼቲቭ ተደማሪ ዐቅም ሆኗል ሲሉም ተናግረዋል። አረንጓዴ ዐሻራ የኢትዮጵያ ልጆች ከፖለቲካ አሰላለፍ አልፈው፣ ከሐሳብ ተቃርኖ ተሻግረው፣ ገጸ ብዙ ልዩነቶችን አሸንፈው ለሀገርና ለትውልድ አስበው ያሳኩት የመተባበር ድል፣ የተጨበጠ ማሳያ ነው ሲሉ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ልጆች ስንተባበር ትርፋችን እልፍ፣ ዕቅዳችንም የተሳካ የሠመረ ይሆናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ የእስከ ዛሬ ድካማችን መደምደሚያ፣ የድላችን መዳረሻ፣ በድል ላይ ቆመን ለሌላ የላቀ ድል የምንነሣበት ልዩ ዓመት ነው ብለዋል። ሁላችንም በሩጫ ትግል ሊያልቅ ሲል እንደሚበረቱት ሊጠናቀቅ ሲል እንደሚፈጥኑት ጀግኖች አትሌቶቻችን ካለፉት ዓመታት አስበልጠን እንትከል! እንበርታ! እንፍጠን ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 8384
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 6825
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 5648
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 5554
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jun 15, 2026 443
በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉የተራሮች ስር ፈርጥ - ወልዲያ የዛሬው የወፍ በረር ምልከታችን የሚጀምረው የተራሮች ስር ፈርጥ በሆነችው ወልዲያ ከተማ በመገኘት ነው። ከደሴ በ120 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውና በረጃጅም ተራሮች የተከበበችው ወልዲያ ከተማ ከነበረችበት ጉስቁልና ወጥታ አሁን ላይ በውበት ፈክታ ትገኛለች። በሳምንቱ በዚህች ከተማ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኮሪደር ልማቷንና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፤ ተዘዋውረውም ጎብኝተዋል። በተለያዩ ታሪካዊና ባህላዊ ትውፊቶች ስሟ ጎልቶ የሚጠራው ወልዲያ እንደ ከዋክብት ፈክታ እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር እየተስፋፉ መሆኑን አንስተው በቀጣይ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ትገሰግሳለች ብለዋል። 👉የሸደር አዳሪ ትምህርት ቤት የሚቀጥለው መዳረሻችን በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን አውበሬ ወረዳ ሼደር ከተማ አዲስ የተገነባውን አዳሪ ትምህርት ቤት መመረቅ ይሆኗል። የትምህርት ቤቱን ግንባታ መርቀው ስራ ያስጀመሩት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ናቸው። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው፤ በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋት የተማረ ትውልድ ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በ138 ሚሊየን ብር የተገነባው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ስራ መጀመሩ ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል። 👉የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የበረራ ቅኝታችን ቀጥሎ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በመስኖ እየለማ ያለ የስንዴ ምርት የመጎብኘት እድል አግኝተናል። በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል መሰብሰብ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። የግብርና ሜካናይዜሽንን በስፋት በመጠቀም እንዲሁም ፈጠራን በማከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ጥረቱ በተሳካ መልኩ መቀጠሉን አንስተዋል። 👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ዓለም አቀፍ ክስተት ነው። ችግሩ በተለይም በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ ይገኛል። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መጠን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ መፍትሄ ለመስጠት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። በዚህ ረገድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት በሚከናወኑ ሥራዎች በምርምር እያገዙ ናቸው። በሂደቱ ውጤታማነት ላይ የሚመክር መድረክ በሰመራ በተደረገበት ወቅት የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ችግሩን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት በምርምርና በማማከር እያገዙ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሰዎች ህገወጥ ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ለህብረተሰቡ እየሰጡ ናቸው። 👉የኢትዮጵያ እያመረተች ነው በአማራ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እና ሌሎችም በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለውጭ ምንዛሬ አይነተኛ የገቢ ምንጭ መሆን አስችሏል ብለዋል። 👉መሶብ በአርባ ምንጭ፣ ዲላ እና ነቀምቴ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት በዚህ ሳምንት አርባ ምንጭ፣ እና ዲላ ከተሞች ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። የመሶብ ማእከላቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል። የዲጅታል አሰራርን በማስፋት ለዜጎች ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። 👉ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩ ስለመሆኑ ያነሳል። በመሆኑም ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን አደራጅቷል። በመሆኑም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በእለቱ ድምፅ መስጠት ካልቻሉት መካከል የሰሜን ምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በፊት ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፃቸውን ሰጥተዋል። በተመሳሳይ በአፋር ክልል እና በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያዎች የሚገኙ ዜጎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል። 👉የመኸር እርሻ ንቅናቄ በሲዳማ ክልል የመኸር እርሻን በንቅናቄ በመምራት የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡና ገበያን የሚያረጋጉ የግብርና ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በንቅናቄ መድረኩ ርእሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት መሬት ጦሙን እንዳያድርና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ እንዲሁም ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠት ምርታማነቱን ማሳካት አስችሏል። ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል የበልግ ሰብልን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። ይህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ በማምረት ገበያን ለማረጋጋትና ለኢንደስትሪዎች ግብአት ለማቅረብ ያስችላል ነው የተባለው። በምርት ዘመኑ የተያዘውን እቅድ ለማሳካትም አመራሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር ለውጤቱ መትጋት እንዳለበትም በውይይቱ ተነስቷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምርጥ ዘር ብዜትን በዓይነት፣ በመጠንና በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ ተችሏል። ቢሮው በግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ እና በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዘር ብዜት ዕቅድ አፈጻጸምና ዝግጅት ላይ ያተኮረ የባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ እንደገለጹት፤ በክልሉ የምርጥ ዘርን በጥራትና በመጠን ለአርሶ አደሩ በወቅቱ በማድረስ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል። ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ለኢንዱስትሪዎች በቂ ግብዓትን ለማቅረብና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር አግዟል። ተግባሩን በማስቀጠልም በ2017/18 የምርት ዘመን በክልሉ ከ2 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ30 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ማምረት መቻሉንም ገልጸዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት
Jun 14, 2026 703
በኢዜአ ዐይን …! በሙሴ መለሰ አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው።በዚህ ሂደት ደግሞ የኢትዮጵያ ድንቅ ስራ የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊትአውራሪነት ይጠቀሳል። መርሐ-ግብሩ የጋራ ነው በሚል ዕሳቤ በርካቶችን በንቃት አሳትፎ ለዓለም የሚደርስ የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ዐሳይቷል። የደን ሽፋን መጠንን አሳድጓል። ይህም በዓየር ንብረት ለውጥ ላይ የራሱን ሚና እያበረከተ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአረንጓዴ ዐሻራ ሚና ልቆ ይነሳል። ይህም የተራቆተ መሬትን ወደ ነበረበት ከመመለስ፣ የውኃ ሀብት አሥተዳደርን ምቹ ከማድረግ እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ጋር የሚያያዝ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብሩ በዕድሜ፣ በጾታ፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሥራ ዘርፎች፣ በኑሮ ደረጃ፣ በሐይማኖት ሳትለይ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች እንዲሳተፉበት በማድረጓ በዘርፉ ስኬታማ ጉዞ ላይ ናት። ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀት ከመሆን አልፎ ለጎረቤቶቿ ችግኝ በመለገስ መርሐ-ግብሩ እንዲስፋፋ እየተጋችም ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ሲናገሩ፤ አረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያ ትላልቅ ነገር አስባ፣ ትላልቅ ነገር ተልማ፣ ትላልቅ ነገር አቅዳ እና ሕዝቦቿን አስተባብራ ማሳካት እንደምትችል ለሌሎቹ ማሳያ ነው ማለታቸውም ከላይ ያነሳነውን ሐሳብ ያዳብረዋል። በተጨማሪም አረንጓዴ ዐሻራ በልዩ ትኩረት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሳይቆራረጥ እየተሠራ መሆኑን፤ በየዓመቱም በሚተከሉ ችግኞች ብዛት፣ በሚተከልበት መሬት ስፋት እና በሚሳተፉ ታታሪዎች ቁጥር እያደገ መሆኑን ያመላክታል። በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች እየወጡ በችግኝ ተከላ መሳተፋቸው የሀገርን የጋራ ራዕይ ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 4376
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 8900
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
ትንታኔዎች
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 163
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ። ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…!
Jun 15, 2026 294
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 4376
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው?
Jun 12, 2026 1324
የጤና ነገር … በዮሐንስ ደርበው የሰው ልጅ ሊሻሻሉ በሚችሉ እና በማይችሉ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ለልብ ህመም ሊጋለጥ እንደሚችል የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የአዋቂ የልብ ሕክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ብርሃኑ ሞገስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የልብ ህመም ከተወሳሰብ ዘላቂ የጤና እክል እስከ ድንገተኛ ኅልፈት ያደርሳል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ሰዎች ማሻሻል በሚችሏቸው (ሞዲፋይብል) እና ማሻሻል በማይችሏቸው (ነን ሞዲፋይብል ወይም ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች) ለልብ ህመም ሊጋለጡ እንደሚችሉ ዶክተር ብርሃኑ ይገልጻሉ። መሻሻል ከሚችሉ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል፤ ከፍተኛ ጭንቀት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ ከፍተኛ የደም ግፊት ህመም (በአግባቡ መድኃኒቱ ካልተወሰደ)፣ተገቢ ያልሆነ የስብ ክምችት፣ ከፍተኛ ውፍረት (ክብደት)፣ በቂ እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ጤናማ አመጋገብ አለመኖር እንዲሁም አብዝቶ ስኳር፣ ጣፋጭና አልኮል መጠቀም የሚሉትን ይጠቅሳሉ፡፡ እንዲሁም ሰዎች ማሻሻል ከማይችሏቸው (ተፈጥሯዊ) አጋላጮች መካከል፤ በቤተሰብ የሚተላለፍ መኖሩን፣ በዕድሜ መጨመር የሚከሰት መሆኑን (ለምሳሌ፡- ወንድ ከ45 ሴት ከ55 ዓመት በላይ ሲሆናቸው ለልብ ህመም ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩን) እንዲሁም ወንዶ ከሴቶች በይበልጥ ለልብ ህመም ተጋላጭ የመሆናቸው አጋጣሚ ሰፊ ሊሆን እንደሚችልም አብራርተዋል፡፡ በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የልብ ህመም ምልክቶች የደረት ውጋት በግራ በኩል ወይም መሐል ላይ፣ ከወትሮው የተለየ ድካም፣ ትንፋሽ ማጠር፣ ከመደበኛው የተለየ የልብ ምት መኖር፣ የሰውነት በተለይም እግር አካባቢ እብጠት፣ ራስን መሳት እና ሳል የልብና ተያያዥ ህመም ምልክት ሊሆኑ እንደሚችሉ አብራርተዋል። የልብን ጤናን ለመጠበቅ በተቻለ መጠን ጤናማ አመጋገብን መከተል እንደሚገባ የሚመክሩት ዶክተር ብርሃኑ፤ አትክልት ማዘውተር፣ ምግብ ሲዘጋጅም ፈሳሽ ዘይት መጠቀም፣ ስኳር፣ ጨው እና ጣፋጭ ነገሮችን መገደብ ከተቻለም ማስወገድ እንደሚገባ ይመክራሉ፡፡ አካላዊ እንቅስቃሴ ማዘውተር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ይህም ብስክሌት መንዳት፣ በእግር እንቅስቃሴ ማድረግ፣ ዋና መዋኘት፣ እስከሚያልብ እና የልብ ምት እስከሚጨምር ብሎም እስከሚደክሙ የአካል ብቃት መሥራት የልብን ጤና ለመጠበቅ አስተዋጽዖ አለው ነው ያሉት፡፡ ጤናማ የሰውነት ክብደት እንዲኖር ማድረግ ተገቢ መሆኑን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ “ቦዲ ማስ ኢንዴክስ (ቢ ኤም አይ)” ከ18 ነጥብ 5 እስከ 25 እንዲሆን ይመከራል ብለዋል፡፡ ሲጋራ አለማጨስ፣ አልኮል አለመጠቀም፣ የስኳር ህመምና ከፍተኛ ደም ግፊት ካለም የመድኃኒት አወሳሰድን አለማስተጓጎል፣ አመጋገብ ላይ ስብ አለማብዛትና አብዝቶ አለመቀመጥ የልብ ህመምን ለመከላከል እንደሚያግዙ ነው ያስረዱት፡፡ ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በታች የሆኑ ጤናማ ሰዎች ከአንድ እስከ ሦስት ዓመት ባሉ ጊዜያት አንድ ጊዜ፣ ዕድሜያቸው ከ45 በላይ የሆኑ በየዓመቱ እንዲሁም የልብ ህመም ያለባቸው እንደሁኔታው በየጊዜው ክትትል እንዲያደርጉም መክረዋል፡፡ ሰዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እራሳቸውን ከልብ ህመም እንዲጠብቁ መክረው፤ ከዚህ ያለፈ ችግር ሲኖር ቶሎ የሕክምና ክትትል ማድረግ እና “ዛሬ ነገ” በማለት ጊዜ እያባከኑ ህመሙ ውስብስብ ደረጃ እስኪደርስ መጠበቅ እንደማይገባቸው አሳስበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ጤና #የልብ_ህመም
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 15014
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 8267
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 14038
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 12490
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 8900
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 7166
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !