ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተተከሉ ችግኞች የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እያደረጉን ነው
Jun 23, 2026 3
አዳኝ አገር ጫቆ፣ሰኔ16/2018(ኢዜአ)፡-በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ቀደም ሲል የተተከሉ ችግኞች የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እያደረጓቸው መሆኑን በምዕራብ ጎንደር ዞን የአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። አርሶ አደሮቹ እንዳሉት ቀደም ሲል በአካባቢያቸው የተከናወኑ የችግኝ ተከላና የእንክብካቤ ሥራዎች የአፈርና የውሃ ሀብትን በመጠበቅ ለአካባቢው ግብርና መነቃቃትና ለተጠቃሚነታቸው ማደግ ጉልህ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። በቀጣይም ይህን ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደገ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል መዘጋጀተቸውን ተናግረዋል። ከወረዳው አርሶ አደሮች መካከል አቶ ሙሉነህ ጀምበር እንደገለጹት፣ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት በአካባቢያቸው ላይ ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት ተጠቃሚ አድርጓቸዋል። ቀደም ሲል በድርቅና በአፈር መሸርሸር ተጎድቶ የነበረው መሬት ማገገሙና የከርሰ ምድር ውሃ መጨመሩ አትክልትና ፍራፍሬ በመስኖ አልምተው ተጠቃሚ ለመሆን እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። ይህን ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም በመጪው ክረምት በወል መሬት ላይ ከሚተክሉት የደን ችግኞች በተጨማሪ በራሳቸው ግማሽ ሄክታር የሚጠጋ መሬት ላይ ማንጎና ዘይቱን ለመትከል ችግኝ ማዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ሌላኛው የወረዳው አርሶ አደር ተሾመ ጫንያለው በበኩላቸው እንዳሉት የአረንጓዴ ልማቱ የእንስሳት መኖ ልማት፣ የንብ ማነብና ሌሎች የገቢ ማስገኛ ሥራዎችን በማከናወን ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ቀደም ሲል የተከሏቸው ማንጎና ሌሎች የቆላ ፍራፍሬ ችግኞች አሁን ላይ ምርት መስጠት በመጀመራቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። አርሶ አደር ታረቀኝ ታከለ በበኩላቸው፣ ዘንድሮ የሚተከሉ ችግኞችን በማዘጋትና የመትከያ ጉድጓዶችን በወቅቱ በመቆፈር በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በመጀሪያው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተከሉት የቡና ችግኝ በአሁኑ ወቅት ምርት መስጠት በመጀመሩ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ከምርቱ ሽያጭ ከ70ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ያገኙትን ጥቅም ለማስፋትም በክረምት በሚካሄደው የችግኝ ተከላ በንቃት ለመሳተፍ የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራውን ቀድመው ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። በምዕራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፈንታሁን ኪሮስ በበኩላቸው እንዳሉት በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል እየተሰራ ነው። ባለፈው ዓመት ከተተከሉ ችግኞች ውስጥ 70 በመቶ የሚሆኑት መጽደቃቸውን አስታውሰው፣ለእዚህም ማህበረሰቡ ለተተከሉ ችግኞች የሚያደርገው እንክብካቤ እያደገ መምጣት አስተዋጾ አድርጓል ብለዋል። በዘንድሮ ክረምትም ለአካባቢው ስነ ምህዳር ተስማሚ የሆኑ የደንና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የቆላ ፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል ሰፊ ዝግጅት መደረጉን አመልክተዋል። ለተከላ ከተዘጋጁ ችግኞች ውስጥ አካሻ ሰኔጋል፣ ሽመል (የቆላ ቀርቀሃ)፣ ኒም፣ ሞሪንጋ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ሙዝ እና ሌሎች እንደሚገኙበት የጠቆሙት አቶ ፈንታሁን፣ ለእዚህም ከ200 ሺህ በላይ ጉድጓዶች ተቆፍረዋል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው የአርሶ አደሩን ችግር የሚፈቱ የምርምር ሥራዎችን ሊያጠናክር ይገባል
Jun 23, 2026 22
አሰላ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦የአርሲ ዩኒቨርሲቲ የአርሶ አደሩን ችግር የሚፈቱ የምርምር ሥራዎች ላይ በማተኮር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የአርሲ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሣ (ዶ/ር) አመለከቱ። ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ1 ሺህ 355 በላይ ተማሪዎች ዛሬ አስመረቀ። በወቅቱም የአርሲ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሣ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ተመራቂዎች የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አሻራቸውን ማኖር አለባቸው። ተመራቂዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እየተጓዘች ባለችበት ወቅት መመረቃቸው ብዙ ስራ ይጠብቃቸዋል ብለዋል። ተመራቂዎች የዜጎችን ሕይወት በመቀየር ሂደት ውስጥ የድርሻቸውን መወጣት አለባቸው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ ዩኒቨርሲቲውም የአርሶ አደሩን ችግር በሚፈቱ የምርምር ሥራዎች ላይ በማተኮር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንዲያስቀጥል አመልክተዋል። በተመሳሳይም ጤናን ጨምሮ በማኅበራዊ አገልግሎቶች እያስገኘ ያለውን ውጤታማ የምርምር ሥራዎችና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፍቃዱ ምትኩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ ይገኛል ብለዋል። በግብርና፣ በጤና፣ በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ውጤታማ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማከናወን ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ተማሪዎች ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ የኢንተርፕረነርሺፕ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ አገልግሎትን ለማስፋፋት በሠራው ሥራ የእናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል ገንብቶ ወደ ሥራ ማስገባቱን ገልጸዋል። የአሰላ ሪፈራል ሆስፒታልን ጨምሮ ከወረቀት ንክኪ ነጻ አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤት ማምጣቱንም አክለዋል።
በአምቦ ወረዳ የሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ለአካባቢው ማህበረሰብ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት እየሰጡ ነው
Jun 23, 2026 26
አምቦ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ወረዳ የሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ለአካባቢው ማህበረሰብ በቅርበት አገልግሎት በመስጠት፣ ህብረተሰቡን ከእንግልትና ከተጨማሪ ወጪ እየታደጉ መሆናቸውን ተገልጋዮች ገለጹ። ከወረዳው ነዋሪዎች መካከል አስተያየታቸውን የሰጡት የሀገር ሽማግሌ አቶ ከበደ በየንሳ፤ ቀደም ሲል ህብረተሰቡ የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታትና ፍትህ ለማግኘት ረጅም ርቀት ይጓዝ እንደነበር አስታውሰዋል። ከዚህ ቀደም ፍትህ ለማግኘት ለከፍተኛ ወጪና እንግልት ይዳርጉ እንደነበር ጠቁመው፣ አሁን ላይ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች በአቅራቢያቸው ስራ መጀመራቸው ችግሩን ቀርፎ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት እንዲያገኙ ማገዛቸውን ገልጸዋል። አቶ ከበደ አክለውም፣ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች መቋቋም በተለይም የመደበኛ ፍርድ ቤቶችን መጨናነቅ ከመቀነሱም በላይ፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ጊዜና ገንዘቡን እንዲቆጥብ ትልቅ እገዛ ማድረጉን አስረድተዋል። ሌላኛዋ የወረዳው ነዋሪ ሃደ ሲንቄ እሸቷ ሚደቅሳ በበኩላቸው፤ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ህብረተሰቡን በቅርበት በማገልገልና አለመግባበት ውስጥ የገቡ ወገኖችን በማስማማት ረገድ የሚሰጡት ፍትህ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። አሰራሩ የአካባቢውን ባህልና የገዳ ሥነ-ሥርዓትን መሠረት ያደረገ በመሆኑ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለው ተቀባይነት ከቀን ወደ ቀን እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። የሰደን ሊባን ይግባኝ ሰሚ ባህላዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እና የኦሮሞ አባገዳዎች ኅብረት ሰብሳቢ አባገዳ ወርቅነህ ተሬሳ፤ ፍርድ ቤቱ የአካባቢውን የዳኝነት ባህልና የገዳ ሥነ-ሥርዓት መሠረት በማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት በበጀት ዓመቱ ወደ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቱ ከመጡ መዝገቦች መካከል 96ቱ ውሳኔ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ባህላዊ ፍርድ ቤቶች የሚሰጡት አገልግሎት የማህበረሰቡን ባህላዊ እሴቶች ጠብቆ ለማቆየት እንደሚረዳ፣ ፍትህን በአጭር ጊዜና ያለ ምንም ክፍያ ለማቅረብ ተመራጭ መሆናቸውን አባገዳ ወርቅነህ ተሬሳ አብራርተዋል።
በ 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ለማምጣት ተዘጋጅተናል
Jun 23, 2026 49
ደሴ፤ ሰኔ 16/ 2018 (ኢዜአ)፡-በዘንድሮ ዓመት በሚካሔደው 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅት ማድረጋቸውን በደሴ ከተማ የሚገኙ ተፈታኝ ተማሪዎች ገለፁ። በከተማዋ ከ2 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደሚወስዱ የከተማው ትምህርት መምሪያ አስታውቋል። ተማሪ ቀመርያ ከማል በደሴ ከተማ የሆጤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን፤ በብሔራዊ ፈተናው የላቀ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ለመግባት ዝግጅት ማድረጓን ለኢዜአ ገልፃለች። ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ የነበረውን ትምህርት በመከለስና የተጠናከረ ጥናት በማድረግ የፈተናውን እለት እየተጠባበቀች እንደምትገኝ ነው የምትገልፀው። በትምህርት ቤቱ የመማር ማስተማር ስራው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዞ ጭምር መካሔዱ ለፈተናው በተሻለ ሁኔታ እንድዘጋጅ አድርጎኛል የምትለው ደግሞ ሌላዋ የዚሁ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው ፅዮን ግርማ ነች ። "ጊዜዬን በአግባቡ በመጠቀም በትጋት እየተዘጋጀሁ ነው" ያለችው ጽዮን ፈተናውን ተረጋግቶ በመስራት ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት ትኩረት ሰጥቼ እየተዘጋጀሁ ነው ብላለች። የመምህር አካለ ወልድ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሰሚራ ክንዱ ፤በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናው የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተወዳዳሪ ለመሆን በቂ ዝግጅት ማድረጓን ነው የገለፀችው ። የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ የምትፈልገው ቦታ ላይ ለመድረስ የራስ ጥረት ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ ሌት ተቀን ጥረት እያደረገች መሆኑዋንም ነው የምትናገረው። የሆጤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ጌታቸው መከተ በበኩላቸው፣ በዘንድሮውዓመት ትምህርት ቤቱ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ላይ የሚያስቀምጣቸው ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል ነው ያሉት። ለተፈታኞች ቤተ መጽሕፍቶችና ቤተ ሙከራዎችን የስራ ሰዓታቸውን ጭምር ከማራዘም ባለፈ የማካካሻ ትምህርትን በመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፍቅር አበበ በበኩላቸው፣ በከተማው 2 ሺህ 854 ተማሪዎችን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደሚወስዱ ገልፀዋል። ተማሪዎቹ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡም ቅድመ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱንም ነው የገለጹት፡፡
ዘላቂ ለውጥ የሚመጣው በጋራ በመቆም ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jun 23, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018(ኢዜአ) ፦ ሀገርን መገንባት በአንድ ትውልድ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን የሁላችንም የጋራና ቀጣይነት ያለው ሥራ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” የተሰኘ ብሔራዊ ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሔደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” በተሰኘው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በመገኘቴ ታላቅ ክብር ይሰማኛል ሲሉ ገልጸዋል። “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ፣ በየደረጃው የተጓዝንበትንና አሁን የደረስንበትን መንገድ መለስ ብዬ እንድቃኘው አድርጎኛል ሲሉም ገልጸዋል። ሀገራችን በራሷ አቅም ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመገንባት፣ ያልተሞከሩ ግዙፍ ልማቶችን በማከናወን በየጊዜው ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረች ትገኛለች ብለዋል። እነዚህ ሁሉ በአጋጣሚ የተገኙ ድሎች አይደሉም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመደመር መንፈስ ላይ ተመስርተው፣ ዘላቂ ለውጥ የሚመጣው በጋራ በመቆም ነው በሚል ጽኑ እምነት የተወሰዱ በቆራጥ ውሳኔዎች የተገኙ ውጤቶች ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም የጀመርናቸው ለውጦች በራሳቸው የመጨረሻ ግብ አይደሉም ይልቁንም ከእኛ በኋላ ለሚመጡት ተከታታይ ትውልዶች የምንጥለው ጠንካራ መሠረት ነው ብለዋል። ሀገርን መገንባት በአንድ ትውልድ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን የሁላችንም የጋራና ቀጣይነት ያለው ሥራ በመሆኑ፤ በዚህ ጽኑ እምነት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይህንን መንፈስ ይዞ ወደፊት እንዲጓዝ፣ የተቀበለውን ወረት አግዝፎ ይበልጥ ወደ ላቀ ከፍታ እንዲያመራ ጥሪዬን አቀርባለሁ ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ፖለቲካ
ብልፅግና ፓርቲ በገባው ቃል መሰረት የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል አለበት
Jun 23, 2026 94
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምፅ ያገኘው ብልፅግና ፓርቲ በገባው ቃል መሰረት የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለፁ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች ብልፅግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በማግኘት ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል። አስተያየታቸው ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ ፓርቲው ከምርጫው በፊት ሕዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎች በቀጣይም አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የተለያዩ ተቋማትን በአንድ ቦታ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ብልሹ አሠራርን ለማስቀረት የተገበረውን የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ማስፋት እንዳለበት ነው ሀሳባቸውን የሰጡት። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ማናዬ ዘነበ እንዳሉት፤ ፓርቲው የሚታይና የሚጨበጥ ስራ በማከናወኑ በርካታ ሕዝብ በድምጹ መርጦታል ይላሉ። አብላጫ ድምፅ ያገኘው ፓርቲ የተሰጠውን ኃላፊነት ግምት ውስጥ በማስገባት በቀጣይ የወጣቶችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎች አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ነው ያሉት። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ብሩክ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ፓርቲው ካሁን ቀደም በኮሪደር ልማትና በወንዝ ዳርቻ የጀመራቸው የልማት ሥራዎች መዲናዋን ሙሉ ለሙሉ የቀየሩ በመሆናቸው ሊጠናከሩ እንደሚገባ ገልፀዋል። ሕዝቡም ካሁን ቀደም ያሳየውን አጋርነት በማጠናከር ከመንግስት ጎን በመቆም ለተሻለች ኢትዮጵያ በጋራ ልንሠራ ይገባል ብለዋል። የብልፅግና ፓርቲ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን ተከትሎ፣ ከምርጫ በፊት ለህዝብ የገባውን ቃል ወደ መሬት ማውረድና በተግባር ማሳየት ይጠበቅበታል ያሉት ደግሞ ከበቡሽ ሽምብር ናቸው። የሕዝብ አመኔታን ለማጽናት እና የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት በማረጋገጥ ሕዝቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የልማት ሥራዎች በትኩረት ሊያከናውን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩትን እንደ ስንዴ ልማትና የሌማት ትሩፋት ያሉ ሥራዎችን ይበልጥ በማስፋት በምግብ ራስን የመቻል ግብን ማረጋገጥና የሸቀጦችን አቅርቦት ማሳደግ እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት ዮሴፍ ታመነ በበኩሉ የምርጫው አሸናፊ ብልፅግና ፓርቲ ከምርጫው በፊት ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች ሲያከናውን መቆየቱ ገልፆ በቀጣይም ይህንኑ ሊያጠናክር ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በተለይም ወጣቱ የልማት ተሳታፊና የስራ እድል ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ውበት ደጉ ፥ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ የተመረጠው ፓርቲ ካሁን ቀደም በተለይም ለወጣቶች ተስፋ ሰጪ የሆኑ ሥራዎች ሲያከናውን መቆየቱን ገልፃ በቀጣይም በላቀ ትጋት ሊሠራ ይገባል ነው ያለችው። የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ የአምራች ዘርፍና ሌሎችም የልማት ፕሮጀክቶችን ማስፋት እንዳለበትም በመጠቆም፥ ፓርቲው የገባውን ቃል በአግባቡ እንዲፈጽም አጋዥ ሚና እንወጣለን ብላለች።
አሜሪካ በቀድሞ ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች ላይ የጣለችው የቪዛ እገዳ ቡድኑ የሚፈጽመውን እኩይ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲያቆም የተላለፈ ግልጽ መልዕክት ነው
Jun 23, 2026 232
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦አሜሪካ በቀድሞ ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን አመራሮችና በቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የጣለችው የቪዛ እገዳ ቡድኑ የሚፈጽመውን ድርጊት በአስቸኳይ እንዲያቆም የተላለፈ ግልጽ መልዕክትና ከፍተኛ ውሳኔ መሆኑን የስምረት ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አልማዝ ገብረጻዲቅ ገለጹ። የቀድሞ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር እና የስምረት ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አልማዝ ገብረጻዲቅ በቅርቡ የተጣለውን የቪዛ እገዳ እና በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ኃላፊዋ እንደገለጹት፣ አሜሪካ በቀድሞው የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የጣለችው የቪዛ እገዳ ቡድኑ ህገወጥ የሆኑ እኩይ እንቅስቃሴዎችን በአስቸኳይ እንዲያቆም የተላለፈ ግልጽ መልዕክት ነው። ይህ ውሳኔ ቡድኑ ቆም ብሎ እንዲያስብና የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል። የቀድሞ ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን በትግራይ ክልል ለጦርነት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የገለጹት የስምረት ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊዋ፤ በክልሉ በከፍተኛ ደረጃ የወጣቶች አፈሳ እየተካሄደ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በክልሉ እምቢ ያሉ ወጣቶች በህገወጥ መንገድ በተዘጋጀ አዋጅ በተደነገገ ቅጣት በአስገዳጅ ሁኔታ ወደ ታጣቂ ቡድኑ እንዲቀላቀሉ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። የታፈሱ ወጣቶች ከአካባቢው እያመለጡ በመውጣት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው፤ ይህንን የአስገዳጅ አፈሳ በመቃወም ወደ አዲስ አበባና ሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች እየተሰደዱ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ጸረ ሰላም ባንዳዎች ከውጭ ጠላት ኃይል ጋር "ፅምዶ" በሚል ስም ኢትዮጵያን ለማዳከም በጋራ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የጠቀሱት የስምረት ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ፤ ይህ የባንዳና የባዳ ቅንጅት አዲስ ጦርነት ለመክፈት እየተዘጋጁ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ አስታውቀዋል። ይህ ፅምዶ የተሰኘው ፕሮጀክት ዋነኛ ዓላማ ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም አጥታ በተረበሸ ሁኔታ ውስጥ እንድትቆይ ማድረግ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የቀድሞው ሕወሃት ጽንፈኛ ቡድን ከሻዕቢያ ጋር ጥምረት በመፍጠር የዚሁ የትርምስ አጀንዳ ተላላኪና መሣሪያ ሆኖ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ስለሆነም የትግራይ ወጣቶች ህገወጥ ስልጣኑን ለማራዘምና ሀገር ለማተራመስ ከባዕዳን ኃይሎች ጋር ትስስር ፈጥሮ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘውን የቀድሞ ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድንን በቃ ማለት እንደሚገባቸው ተናግረዋል።
የምርጫ አሸናፊው ብልጽግና ፓርቲ ለህዝብ የገባውን ቃል ተግባራዊ በማድረግ ዘላቂ ልማትን ሊያረጋግጥ ይገባል
Jun 23, 2026 188
ጋምቤላ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡-በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሸናፊ የሆነው የብልጽግና ፓርቲ ለሕዝብ የገባውን ቃል በተግባር በመተርጎም ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ በትጋት መስራት እንዳለበት የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በተደረገው ለሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በማግኘት ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማስታወቁ ይታወሳል። የምርጫውን ውጤት በማስመልከት የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት በ7ኛው ጠቅላላ የምርጫ አሸናፊው ብልጽግና ፓርቲ የገባውን ቃል ተግባራዊ በማድረግ ለህዝቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ሊተጋ ይገባል ብለዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ አንዳርጌ ዋሲሁን፤አሸናፊው ፓርቲ በማኒፌስቶውና በፕሮግራሙ ለህዝብ የገባውን ቃል ተግባራዊ በማድረግ በህዝቡ ለሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ህዝቡም ከመንግስት ጎን በመሆን በምርጫው ያሳየው ተሳትፎ በልማቱ ለመድገም አብሮነቱን በማጠናከር በአንድነት ሊሰራ እንደሚገባም ገልጸዋል። በሀገራዊ ምርጫው አሸናፊ የሆነው የብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማስቀጠል የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል ያለው ደግሞ ወጣት ኡሞድ ኡሞድ ነው። በተለይም እንደ ጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት የታዩት የልማት ጅማሮዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እንሻለን ለዚህም ከመንግስት ጎን እንቆማለን ብለዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ዘለቀ ደበሌ በሰጡት አስተያየት አሸናፊው ፓርቲ የህዝቦችን አንድነትና አብሮነት በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን የማረጋገጥ ስራው ትኩረቱ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ፓርቲው በቀጣይ አምስት ዓመታት የህዝቦችን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጥበት ጊዜ ሊሆን ይገባል ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በፓርቲው ማኒፌስቶና ፕሮግራሞች ለህዝቡ የተገለጹ እቅዶችን ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ የልማት ውጤት ለማስመዝገብ ሊሰራ ይገባል ያሉት ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ወጣት ካማ ኡቦንግ ነው። የብልጽግና ፓርቲ በምርጫው ማሸነፉ ቀደም ሲል የጀመራቸውን ስራዎች ስኬታማ ለማድረግ ምቹ አጋጣሚ ይፈጥራል ያለው ወጣቱ፤ እኛም እንደ ወጣት ከጎኑ ሆነን እንተጋለን ብሏል።
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ
Jun 22, 2026 1076
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ (ዶ/ር)ን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ውይይቱን አስመልክቶ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ውይይቱ ኢትዮጵያ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ስደተኞችን በማስተናገድ ረገድ ለምትጫወተው ወሳኝ ሚና ድርጅታቸው ያለውን አድናቆትና እውቅና ለመግለጽ ትልቅ አጋጣሚ መፍጠሩን ገልጸዋል። በተለይም ሀገሪቱ ስደተኞችን በብሔራዊ ሥርዓቱ ውስጥ ለማካተትና በሰብአዊ እርዳታ ላይ ብቻ ጥገኞች እንዳይሆኑ ለመርዳት በቅርቡ ይፋ ያደረገችውን የማካተት ፍኖተ ካርታን በአብነት ጠቅሰዋል። በፍኖተ ካርታው የትግበራ ሂደት ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም የጋራ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል፣ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ ኢትዮጵያ በቅርቡ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት በማጠናቀቋ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው፤ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክትም አስተላልፈዋል።
የብልፅግና ፓርቲ የሀገሪቱን ልማት ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ የጋራ ምክር ቤቱ አብሮ ለመሥራት ዝግጁ ነው
Jun 22, 2026 863
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የምርጫ አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ የከተማዋንና የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ፣ የጋራ ምክር ቤቱ በነቃ ተሳትፎ፣ በገንቢ ሂስና በአማራጭ ሃሳቦች አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቅን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። የጋራ ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተጠናቆ የብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ በማግኘት ማሸነፉን አስታውቋል። ምክር ቤቱ ይህ ምርጫ የከተማዋንና የሀገሪቱን የፖለቲካ ብስለት እንዲሁም የሕዝብን የሉዓላዊነት ስልጣን ያረጋገጠ ታሪካዊ መድረክ መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን ገልጾ፣ በሕዝብ ነፃ ውሳኔ አሸናፊ ለሆነው ለብልፅግና ፓርቲ እና በውድድሩ ተሳትፈው የምክር ቤት ወንበር ላገኙ ፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ምክር ቤቱ ስም ልባዊ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ታሪካዊው ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅና የዲሞክራሲ ባህል እንዲጎለብት በውድድሩ የተሳተፉ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ላበረከቱት አዎንታዊና ታሪካዊ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ የላቀ ምስጋና አቅርቧል። በምክር ቤቱ ስር የሚንቀሳቀሱም ሆኑ በምርጫው የተሳተፉ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሂደቱ ላሳዩት ከፍተኛ የፖለቲካ ጨዋነት፣ለሰላማዊ የሃሳብ ፉክክርና ለሕግ የበላይነት መገዛት የሚደነቅ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው፣ይህ የሰለጠነ አካሄድ ለዜጎች ሰፊ የአማራጭ አድማስ ከመፍጠሩም በላይ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ቁልፍ ሚና መጫወቱን አስገንዝቧል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በነፃነትና በሰላማዊ መንገድ ወጥተው የሰጡትን ድምፅና ያሳዩትን ምርጫ በሙሉ ልብ በመቀበል፣ ለሕዝብ ድምፅ ያለውን ፍጹም ክብርና እውቅና አረጋግጧል። የምርጫው ምዕራፍ በተሳካ ሁኔታ ቢጠናቀቅም፣የሀገር ግንባታ እና የሕዝብ አገልግሎት ቀጣይነት ያለው የጋራ ሃላፊነት በመሆኑ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ምክር ቤቱ አሳስቧል። አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ የከተማዋንና የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ፣ የጋራ ምክር ቤቱ በነቃ ተሳትፎ፣ በገንቢ ሂስና በአማራጭ ሃሳቦች አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ምክር ቤቱ በውድድሩ ተሳትፈው የምክር ቤት ወንበር ላገኙ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች፣ እንዲሁም በድጋሚ ለብልፅግና ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች እንኳን ደስ ያላችሁ ብሏል። መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ባለድርሻ አካላት ለሰላማዊው የምርጫ ሂደት ስኬት ላደረጉት ታሪካዊ አስተዋጽኦም ምስጋናውን አቅርቧል።
የኢትዮጵያ እና የዩናይትድ ኪንግደም ግንኙነት ይበልጥ ሊጠናከር ይገባል-ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Jun 22, 2026 802
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የኢትዮጵያና የዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል። በለንደን ከተማ የሲዳራ ግሩፕ (Sidara Group) ያዘጋጀው እንዲሁም በሌበር አፍሪካ ኔትወርክ (Labour African Network) እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም ኤምባሲ በጋራ በተሰናዳው የዲፕሎማቲክ እራት መርሐ ግብር ተካሄዷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም የዕድገትና ብልጽግና አዳዲስ ዕድሎችን ለመጠቀም የውይይት እና የትብብር መድረኮች ወሳኝ ሚና አላቸው። የኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም ግንኙነት በመንግሥት ተቋማት መካከል ብቻ የተገደበ እንዳልሆነ ገልጸዋል። ትብብሩ በንግድ ድርጅቶች፣ በትምህርት ተቋማት፣ በዲያስፖራ ማህበረሰቦች እና በሁለቱ ሀገራት ዜጎች መካከል ባለው ዘላቂ ትስስር ላይ የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትም ለጠንካራ እና ዘላቂ አጋርነት ዋነኛው ምሰሶ ነው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ወቅታዊ የሪፎርም አጀንዳ እና የረጅም ጊዜ የልማት ትልሞችን አንስተዋል። በተለይም ኢኮኖሚውን ለማጠናከር፣ ለወጣቱ ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንዲሁም አካታች እና ዘላቂ ዕድገትን ለማስፈን እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሕዝብ የአይበገሬነት አቅምና በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለውን አዲስ የተስፋ መንፈስ በመጥቀስም የወደፊቱ ጊዜ ብሩህ እንደሚሆን ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል በንግድ፣በኢንቨስትመንት፣በትምህርት፣ በምርምር፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራ (ኢኖቬሽን) እና በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም አቅም ዙሪያ ሰፊ የትብብር ዕድሎች መኖራቸውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰበ የመጣውን ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ በአግባቡ ለመወጣት እና ለሁለቱም ሀገራት ዜጎች ተጨባጭ ጥቅሞችን ለማስገኘት ጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት መፍጠር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም አሳስበዋል። የሌበር አፍሪካ ኔትወርክ (LAN) ሊቀመንበር ኤርነስት አምቤ በንግግራቸው ኔትወርኩ፤ የአፍሪካ ድምጽ በዩናይትድ ኪንግደም የፖሊሲ ቀረጻ፣ የንግድ እና የዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ ጎልቶ እንዲሰማ በማድረግ ረገድ የተጫወተውን ጉልህ ሚና አድንቀዋል። አያይዘውም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከአፍሪካ ትላልቅ እና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ገበያዎች አንዱ መሆኑን በልዩ ሁኔታ አንስተዋል። በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን በበኩላቸው፥ የዲፕሎማሲ ሁነቱ እየተጠናከረ የመጣው የሀገራቱ የንግድ፣የኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ትብብር ለማስፋት መልካም አጋጣሚን መፍጠሩን ገልጸዋል። ዩናይትድ ኪንግደም ከኢትዮጵያ እና ከአጠቃላይ አፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ አጋርነት ማደግ አዳዲስ ዕድሎችን፣ የጋራ ብልጽግናን እና አካታች ዘላቂ ዕድገትን ለማምጣት እንደሚያስችል መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ብልፅግና ፓርቲ በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Jun 22, 2026 732
ጅማ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ይፋ ባደረገው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት፣ ብልፅግና ፓርቲ በአብላጫ የምርክ ቤት መቀመጫ ማግኘቱ ይታወቃል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ታመነ ኃይሉ፤ ፓርቲው የጀመራቸውን ትልልቅ ፕሮጀክቶችና በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ፓርቲው ከዚህ ቀደም ያከናወናቸው ሰው-ተኮር ልማቶች አገሪቱን ከድህነት ለማውጣት ከፍተኛ አቅም ማበርከታቸውን የጠቀሱት አቶ ታመነ፤ በቀጣይም ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ርብርብ ሕዝቡና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ ይሰራሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሙደሲር መሐመድ በበኩላቸው፤ ፓርቲው ያቀዳቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ለሕዝብ ተጠቃሚነት ለማዋል ከታችኛው መዋቅር ጀምሮ ሙስናን የመታገል ተግባሩን ማጠናከር እንዳለበት ጠቁመዋል። ለዚህም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አሰራር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት፣ የሙስና መከላከያ ስልቶችን ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል። የአገርን ሰላም ማስከበርና ልማትን ማፅናት ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም ያሉት አቶ ሙደሲር፤ ጉዳዩ የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ እሳቸውም የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ሕዝቡ በምርጫ ሥልጣን የሰጠው ፓርቲ የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠርና ሕገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል የሚያደርገውን ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ደግሞ አቶ መልካሙ ቡላ እና አቶ በፀጋው አበራ ናቸው። አስተያየት ሰጪዎቹ የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ማንኛውንም ጥረት በንቃት በመደገፍ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አስታውቀዋል።
ምርጫው ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው-አብን
Jun 22, 2026 747
አዲስ አበባ፤ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፡-7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው ሲል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ገለጸ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ትናንት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫውን ሂደት ስኬታማነት በመግለጽ፤ ውጤቱን በጸጋ መቀበላቸውን እና በአብላጫ ድምጽ ላሸነፈው ብልጽግና ፓርቲም የመልካም ምኞት መግለጫ እያስተላለፉ ነው። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በበኩሉ ባወጣው መግለጫም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው ብሏል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ ወደ ተሻለ የፖለቲካ እና የማኅበረ-ኢኮኖሚ ምዕራፍ ለመሻገር ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ውሳኔ መሆኑንም አመላክቷል። የተመዘገበው ስኬት የማህበረሰባችን የአርቆ አሳቢነት ትሩፋት በመሆኑ ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባም ነው ብሏል በመግለጫው፡፡ ምርጫው ሕዝባችን ፈተናዎችን ተቋቁሞ በታሪክ የሚዘከር የአይበገሬነት ታሪክ የጻፈበት፣ ለዘላቂ ሰላምና እድገት የሚበጅ የፖለቲካ ባህል አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ ያደረገበት፣ በዋናነት የማኅበረ-ፖለቲካ ግብረ-ገብ እሴቶች ተቃራኒ የሆኑ ጯሂና እኩይ ድምጸቶችን ማሸነፍ የቻለበት፣ ለሰላም ሲባል ዋጋ የመክፈል ቁርጠኝነት የታየበትና ዋጋ የተከፈለበት መሆኑንም ነው የገለጸው። ሕዝብን ማሸነፍ አይቻልምና ድሉ የሰላም ወዳዱ ሕዝብ ሆኗልም ነው ያለው። ምርጫው ለውጫዊ የኢትዮጵያ ጠላቶችም ተስፋ ያስቆረጠ ክስተት መሆኑንም አብን ገልጿል። ዳያስፖራው ልማቶችንና የሰላም እንቅስቃሴዎችን እንዲደግፍ እንዲሁም ለሀገራዊ መረጋጋት ፋይዳ ከሌላቸው አጀንዳዎች ራሱን እንዲያርቅ አብን ጥሪ አቅርቧል። በመጨረሻም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምጽ ላገኘው ብልጽግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልካም ምኞቱን ገልጾ፤መጭው ጊዜ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ሁለንተናዊ ምዕራፍ የምናሻግርበት ነው ሲል ገልጿል።
ፖለቲካ
ብልፅግና ፓርቲ በገባው ቃል መሰረት የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል አለበት
Jun 23, 2026 94
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምፅ ያገኘው ብልፅግና ፓርቲ በገባው ቃል መሰረት የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለፁ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች ብልፅግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በማግኘት ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል። አስተያየታቸው ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ ፓርቲው ከምርጫው በፊት ሕዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎች በቀጣይም አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የተለያዩ ተቋማትን በአንድ ቦታ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ብልሹ አሠራርን ለማስቀረት የተገበረውን የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ማስፋት እንዳለበት ነው ሀሳባቸውን የሰጡት። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ማናዬ ዘነበ እንዳሉት፤ ፓርቲው የሚታይና የሚጨበጥ ስራ በማከናወኑ በርካታ ሕዝብ በድምጹ መርጦታል ይላሉ። አብላጫ ድምፅ ያገኘው ፓርቲ የተሰጠውን ኃላፊነት ግምት ውስጥ በማስገባት በቀጣይ የወጣቶችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎች አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ነው ያሉት። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ብሩክ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ፓርቲው ካሁን ቀደም በኮሪደር ልማትና በወንዝ ዳርቻ የጀመራቸው የልማት ሥራዎች መዲናዋን ሙሉ ለሙሉ የቀየሩ በመሆናቸው ሊጠናከሩ እንደሚገባ ገልፀዋል። ሕዝቡም ካሁን ቀደም ያሳየውን አጋርነት በማጠናከር ከመንግስት ጎን በመቆም ለተሻለች ኢትዮጵያ በጋራ ልንሠራ ይገባል ብለዋል። የብልፅግና ፓርቲ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን ተከትሎ፣ ከምርጫ በፊት ለህዝብ የገባውን ቃል ወደ መሬት ማውረድና በተግባር ማሳየት ይጠበቅበታል ያሉት ደግሞ ከበቡሽ ሽምብር ናቸው። የሕዝብ አመኔታን ለማጽናት እና የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት በማረጋገጥ ሕዝቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የልማት ሥራዎች በትኩረት ሊያከናውን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩትን እንደ ስንዴ ልማትና የሌማት ትሩፋት ያሉ ሥራዎችን ይበልጥ በማስፋት በምግብ ራስን የመቻል ግብን ማረጋገጥና የሸቀጦችን አቅርቦት ማሳደግ እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት ዮሴፍ ታመነ በበኩሉ የምርጫው አሸናፊ ብልፅግና ፓርቲ ከምርጫው በፊት ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች ሲያከናውን መቆየቱ ገልፆ በቀጣይም ይህንኑ ሊያጠናክር ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በተለይም ወጣቱ የልማት ተሳታፊና የስራ እድል ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ውበት ደጉ ፥ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ የተመረጠው ፓርቲ ካሁን ቀደም በተለይም ለወጣቶች ተስፋ ሰጪ የሆኑ ሥራዎች ሲያከናውን መቆየቱን ገልፃ በቀጣይም በላቀ ትጋት ሊሠራ ይገባል ነው ያለችው። የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ የአምራች ዘርፍና ሌሎችም የልማት ፕሮጀክቶችን ማስፋት እንዳለበትም በመጠቆም፥ ፓርቲው የገባውን ቃል በአግባቡ እንዲፈጽም አጋዥ ሚና እንወጣለን ብላለች።
አሜሪካ በቀድሞ ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች ላይ የጣለችው የቪዛ እገዳ ቡድኑ የሚፈጽመውን እኩይ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲያቆም የተላለፈ ግልጽ መልዕክት ነው
Jun 23, 2026 232
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦አሜሪካ በቀድሞ ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን አመራሮችና በቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የጣለችው የቪዛ እገዳ ቡድኑ የሚፈጽመውን ድርጊት በአስቸኳይ እንዲያቆም የተላለፈ ግልጽ መልዕክትና ከፍተኛ ውሳኔ መሆኑን የስምረት ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አልማዝ ገብረጻዲቅ ገለጹ። የቀድሞ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር እና የስምረት ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አልማዝ ገብረጻዲቅ በቅርቡ የተጣለውን የቪዛ እገዳ እና በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ኃላፊዋ እንደገለጹት፣ አሜሪካ በቀድሞው የሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የጣለችው የቪዛ እገዳ ቡድኑ ህገወጥ የሆኑ እኩይ እንቅስቃሴዎችን በአስቸኳይ እንዲያቆም የተላለፈ ግልጽ መልዕክት ነው። ይህ ውሳኔ ቡድኑ ቆም ብሎ እንዲያስብና የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል። የቀድሞ ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድን በትግራይ ክልል ለጦርነት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የገለጹት የስምረት ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊዋ፤ በክልሉ በከፍተኛ ደረጃ የወጣቶች አፈሳ እየተካሄደ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በክልሉ እምቢ ያሉ ወጣቶች በህገወጥ መንገድ በተዘጋጀ አዋጅ በተደነገገ ቅጣት በአስገዳጅ ሁኔታ ወደ ታጣቂ ቡድኑ እንዲቀላቀሉ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። የታፈሱ ወጣቶች ከአካባቢው እያመለጡ በመውጣት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው፤ ይህንን የአስገዳጅ አፈሳ በመቃወም ወደ አዲስ አበባና ሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች እየተሰደዱ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ጸረ ሰላም ባንዳዎች ከውጭ ጠላት ኃይል ጋር "ፅምዶ" በሚል ስም ኢትዮጵያን ለማዳከም በጋራ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የጠቀሱት የስምረት ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ፤ ይህ የባንዳና የባዳ ቅንጅት አዲስ ጦርነት ለመክፈት እየተዘጋጁ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ አስታውቀዋል። ይህ ፅምዶ የተሰኘው ፕሮጀክት ዋነኛ ዓላማ ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም አጥታ በተረበሸ ሁኔታ ውስጥ እንድትቆይ ማድረግ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የቀድሞው ሕወሃት ጽንፈኛ ቡድን ከሻዕቢያ ጋር ጥምረት በመፍጠር የዚሁ የትርምስ አጀንዳ ተላላኪና መሣሪያ ሆኖ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ስለሆነም የትግራይ ወጣቶች ህገወጥ ስልጣኑን ለማራዘምና ሀገር ለማተራመስ ከባዕዳን ኃይሎች ጋር ትስስር ፈጥሮ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘውን የቀድሞ ሕወሓት ጽንፈኛ ቡድንን በቃ ማለት እንደሚገባቸው ተናግረዋል።
የምርጫ አሸናፊው ብልጽግና ፓርቲ ለህዝብ የገባውን ቃል ተግባራዊ በማድረግ ዘላቂ ልማትን ሊያረጋግጥ ይገባል
Jun 23, 2026 188
ጋምቤላ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡-በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሸናፊ የሆነው የብልጽግና ፓርቲ ለሕዝብ የገባውን ቃል በተግባር በመተርጎም ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ በትጋት መስራት እንዳለበት የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በተደረገው ለሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በማግኘት ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማስታወቁ ይታወሳል። የምርጫውን ውጤት በማስመልከት የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት በ7ኛው ጠቅላላ የምርጫ አሸናፊው ብልጽግና ፓርቲ የገባውን ቃል ተግባራዊ በማድረግ ለህዝቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ሊተጋ ይገባል ብለዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ አንዳርጌ ዋሲሁን፤አሸናፊው ፓርቲ በማኒፌስቶውና በፕሮግራሙ ለህዝብ የገባውን ቃል ተግባራዊ በማድረግ በህዝቡ ለሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ህዝቡም ከመንግስት ጎን በመሆን በምርጫው ያሳየው ተሳትፎ በልማቱ ለመድገም አብሮነቱን በማጠናከር በአንድነት ሊሰራ እንደሚገባም ገልጸዋል። በሀገራዊ ምርጫው አሸናፊ የሆነው የብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማስቀጠል የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል ያለው ደግሞ ወጣት ኡሞድ ኡሞድ ነው። በተለይም እንደ ጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት የታዩት የልማት ጅማሮዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እንሻለን ለዚህም ከመንግስት ጎን እንቆማለን ብለዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ዘለቀ ደበሌ በሰጡት አስተያየት አሸናፊው ፓርቲ የህዝቦችን አንድነትና አብሮነት በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን የማረጋገጥ ስራው ትኩረቱ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ፓርቲው በቀጣይ አምስት ዓመታት የህዝቦችን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጥበት ጊዜ ሊሆን ይገባል ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በፓርቲው ማኒፌስቶና ፕሮግራሞች ለህዝቡ የተገለጹ እቅዶችን ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ የልማት ውጤት ለማስመዝገብ ሊሰራ ይገባል ያሉት ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ወጣት ካማ ኡቦንግ ነው። የብልጽግና ፓርቲ በምርጫው ማሸነፉ ቀደም ሲል የጀመራቸውን ስራዎች ስኬታማ ለማድረግ ምቹ አጋጣሚ ይፈጥራል ያለው ወጣቱ፤ እኛም እንደ ወጣት ከጎኑ ሆነን እንተጋለን ብሏል።
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ
Jun 22, 2026 1076
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ (ዶ/ር)ን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ውይይቱን አስመልክቶ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ውይይቱ ኢትዮጵያ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ስደተኞችን በማስተናገድ ረገድ ለምትጫወተው ወሳኝ ሚና ድርጅታቸው ያለውን አድናቆትና እውቅና ለመግለጽ ትልቅ አጋጣሚ መፍጠሩን ገልጸዋል። በተለይም ሀገሪቱ ስደተኞችን በብሔራዊ ሥርዓቱ ውስጥ ለማካተትና በሰብአዊ እርዳታ ላይ ብቻ ጥገኞች እንዳይሆኑ ለመርዳት በቅርቡ ይፋ ያደረገችውን የማካተት ፍኖተ ካርታን በአብነት ጠቅሰዋል። በፍኖተ ካርታው የትግበራ ሂደት ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም የጋራ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል፣ ኮሚሽነር በርሃም ሳሊህ ኢትዮጵያ በቅርቡ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት በማጠናቀቋ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው፤ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክትም አስተላልፈዋል።
የብልፅግና ፓርቲ የሀገሪቱን ልማት ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ የጋራ ምክር ቤቱ አብሮ ለመሥራት ዝግጁ ነው
Jun 22, 2026 863
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የምርጫ አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ የከተማዋንና የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ፣ የጋራ ምክር ቤቱ በነቃ ተሳትፎ፣ በገንቢ ሂስና በአማራጭ ሃሳቦች አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቅን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። የጋራ ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተጠናቆ የብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ በማግኘት ማሸነፉን አስታውቋል። ምክር ቤቱ ይህ ምርጫ የከተማዋንና የሀገሪቱን የፖለቲካ ብስለት እንዲሁም የሕዝብን የሉዓላዊነት ስልጣን ያረጋገጠ ታሪካዊ መድረክ መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን ገልጾ፣ በሕዝብ ነፃ ውሳኔ አሸናፊ ለሆነው ለብልፅግና ፓርቲ እና በውድድሩ ተሳትፈው የምክር ቤት ወንበር ላገኙ ፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ምክር ቤቱ ስም ልባዊ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። ታሪካዊው ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅና የዲሞክራሲ ባህል እንዲጎለብት በውድድሩ የተሳተፉ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ላበረከቱት አዎንታዊና ታሪካዊ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ የላቀ ምስጋና አቅርቧል። በምክር ቤቱ ስር የሚንቀሳቀሱም ሆኑ በምርጫው የተሳተፉ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሂደቱ ላሳዩት ከፍተኛ የፖለቲካ ጨዋነት፣ለሰላማዊ የሃሳብ ፉክክርና ለሕግ የበላይነት መገዛት የሚደነቅ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው፣ይህ የሰለጠነ አካሄድ ለዜጎች ሰፊ የአማራጭ አድማስ ከመፍጠሩም በላይ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ቁልፍ ሚና መጫወቱን አስገንዝቧል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በነፃነትና በሰላማዊ መንገድ ወጥተው የሰጡትን ድምፅና ያሳዩትን ምርጫ በሙሉ ልብ በመቀበል፣ ለሕዝብ ድምፅ ያለውን ፍጹም ክብርና እውቅና አረጋግጧል። የምርጫው ምዕራፍ በተሳካ ሁኔታ ቢጠናቀቅም፣የሀገር ግንባታ እና የሕዝብ አገልግሎት ቀጣይነት ያለው የጋራ ሃላፊነት በመሆኑ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ምክር ቤቱ አሳስቧል። አሸናፊው የብልፅግና ፓርቲ የከተማዋንና የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ላይ፣ የጋራ ምክር ቤቱ በነቃ ተሳትፎ፣ በገንቢ ሂስና በአማራጭ ሃሳቦች አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ምክር ቤቱ በውድድሩ ተሳትፈው የምክር ቤት ወንበር ላገኙ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች፣ እንዲሁም በድጋሚ ለብልፅግና ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች እንኳን ደስ ያላችሁ ብሏል። መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ባለድርሻ አካላት ለሰላማዊው የምርጫ ሂደት ስኬት ላደረጉት ታሪካዊ አስተዋጽኦም ምስጋናውን አቅርቧል።
የኢትዮጵያ እና የዩናይትድ ኪንግደም ግንኙነት ይበልጥ ሊጠናከር ይገባል-ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Jun 22, 2026 802
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የኢትዮጵያና የዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል። በለንደን ከተማ የሲዳራ ግሩፕ (Sidara Group) ያዘጋጀው እንዲሁም በሌበር አፍሪካ ኔትወርክ (Labour African Network) እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም ኤምባሲ በጋራ በተሰናዳው የዲፕሎማቲክ እራት መርሐ ግብር ተካሄዷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም የዕድገትና ብልጽግና አዳዲስ ዕድሎችን ለመጠቀም የውይይት እና የትብብር መድረኮች ወሳኝ ሚና አላቸው። የኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም ግንኙነት በመንግሥት ተቋማት መካከል ብቻ የተገደበ እንዳልሆነ ገልጸዋል። ትብብሩ በንግድ ድርጅቶች፣ በትምህርት ተቋማት፣ በዲያስፖራ ማህበረሰቦች እና በሁለቱ ሀገራት ዜጎች መካከል ባለው ዘላቂ ትስስር ላይ የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትም ለጠንካራ እና ዘላቂ አጋርነት ዋነኛው ምሰሶ ነው ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ወቅታዊ የሪፎርም አጀንዳ እና የረጅም ጊዜ የልማት ትልሞችን አንስተዋል። በተለይም ኢኮኖሚውን ለማጠናከር፣ ለወጣቱ ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንዲሁም አካታች እና ዘላቂ ዕድገትን ለማስፈን እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሕዝብ የአይበገሬነት አቅምና በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለውን አዲስ የተስፋ መንፈስ በመጥቀስም የወደፊቱ ጊዜ ብሩህ እንደሚሆን ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል በንግድ፣በኢንቨስትመንት፣በትምህርት፣ በምርምር፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራ (ኢኖቬሽን) እና በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም አቅም ዙሪያ ሰፊ የትብብር ዕድሎች መኖራቸውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰበ የመጣውን ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ በአግባቡ ለመወጣት እና ለሁለቱም ሀገራት ዜጎች ተጨባጭ ጥቅሞችን ለማስገኘት ጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት መፍጠር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም አሳስበዋል። የሌበር አፍሪካ ኔትወርክ (LAN) ሊቀመንበር ኤርነስት አምቤ በንግግራቸው ኔትወርኩ፤ የአፍሪካ ድምጽ በዩናይትድ ኪንግደም የፖሊሲ ቀረጻ፣ የንግድ እና የዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ ጎልቶ እንዲሰማ በማድረግ ረገድ የተጫወተውን ጉልህ ሚና አድንቀዋል። አያይዘውም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከአፍሪካ ትላልቅ እና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ገበያዎች አንዱ መሆኑን በልዩ ሁኔታ አንስተዋል። በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን በበኩላቸው፥ የዲፕሎማሲ ሁነቱ እየተጠናከረ የመጣው የሀገራቱ የንግድ፣የኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ትብብር ለማስፋት መልካም አጋጣሚን መፍጠሩን ገልጸዋል። ዩናይትድ ኪንግደም ከኢትዮጵያ እና ከአጠቃላይ አፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ አጋርነት ማደግ አዳዲስ ዕድሎችን፣ የጋራ ብልጽግናን እና አካታች ዘላቂ ዕድገትን ለማምጣት እንደሚያስችል መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ብልፅግና ፓርቲ በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
Jun 22, 2026 732
ጅማ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ይፋ ባደረገው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት፣ ብልፅግና ፓርቲ በአብላጫ የምርክ ቤት መቀመጫ ማግኘቱ ይታወቃል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ታመነ ኃይሉ፤ ፓርቲው የጀመራቸውን ትልልቅ ፕሮጀክቶችና በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ቃል የገባቸውን ተግባራት ለመፈጸም በሚያደርገው እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ፓርቲው ከዚህ ቀደም ያከናወናቸው ሰው-ተኮር ልማቶች አገሪቱን ከድህነት ለማውጣት ከፍተኛ አቅም ማበርከታቸውን የጠቀሱት አቶ ታመነ፤ በቀጣይም ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ርብርብ ሕዝቡና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ ይሰራሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሙደሲር መሐመድ በበኩላቸው፤ ፓርቲው ያቀዳቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ለሕዝብ ተጠቃሚነት ለማዋል ከታችኛው መዋቅር ጀምሮ ሙስናን የመታገል ተግባሩን ማጠናከር እንዳለበት ጠቁመዋል። ለዚህም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አሰራር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማደራጀት፣ የሙስና መከላከያ ስልቶችን ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል። የአገርን ሰላም ማስከበርና ልማትን ማፅናት ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም ያሉት አቶ ሙደሲር፤ ጉዳዩ የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ እሳቸውም የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ሕዝቡ በምርጫ ሥልጣን የሰጠው ፓርቲ የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠርና ሕገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል የሚያደርገውን ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ደግሞ አቶ መልካሙ ቡላ እና አቶ በፀጋው አበራ ናቸው። አስተያየት ሰጪዎቹ የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ማንኛውንም ጥረት በንቃት በመደገፍ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አስታውቀዋል።
ምርጫው ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው-አብን
Jun 22, 2026 747
አዲስ አበባ፤ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፡-7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው ሲል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ገለጸ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ትናንት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫውን ሂደት ስኬታማነት በመግለጽ፤ ውጤቱን በጸጋ መቀበላቸውን እና በአብላጫ ድምጽ ላሸነፈው ብልጽግና ፓርቲም የመልካም ምኞት መግለጫ እያስተላለፉ ነው። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በበኩሉ ባወጣው መግለጫም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ለሰላም ሲባል ውድ ዋጋ ከፍሎ ያሸነፈበት ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ነው ብሏል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ ወደ ተሻለ የፖለቲካ እና የማኅበረ-ኢኮኖሚ ምዕራፍ ለመሻገር ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ውሳኔ መሆኑንም አመላክቷል። የተመዘገበው ስኬት የማህበረሰባችን የአርቆ አሳቢነት ትሩፋት በመሆኑ ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባም ነው ብሏል በመግለጫው፡፡ ምርጫው ሕዝባችን ፈተናዎችን ተቋቁሞ በታሪክ የሚዘከር የአይበገሬነት ታሪክ የጻፈበት፣ ለዘላቂ ሰላምና እድገት የሚበጅ የፖለቲካ ባህል አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ ያደረገበት፣ በዋናነት የማኅበረ-ፖለቲካ ግብረ-ገብ እሴቶች ተቃራኒ የሆኑ ጯሂና እኩይ ድምጸቶችን ማሸነፍ የቻለበት፣ ለሰላም ሲባል ዋጋ የመክፈል ቁርጠኝነት የታየበትና ዋጋ የተከፈለበት መሆኑንም ነው የገለጸው። ሕዝብን ማሸነፍ አይቻልምና ድሉ የሰላም ወዳዱ ሕዝብ ሆኗልም ነው ያለው። ምርጫው ለውጫዊ የኢትዮጵያ ጠላቶችም ተስፋ ያስቆረጠ ክስተት መሆኑንም አብን ገልጿል። ዳያስፖራው ልማቶችንና የሰላም እንቅስቃሴዎችን እንዲደግፍ እንዲሁም ለሀገራዊ መረጋጋት ፋይዳ ከሌላቸው አጀንዳዎች ራሱን እንዲያርቅ አብን ጥሪ አቅርቧል። በመጨረሻም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምጽ ላገኘው ብልጽግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልካም ምኞቱን ገልጾ፤መጭው ጊዜ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ሁለንተናዊ ምዕራፍ የምናሻግርበት ነው ሲል ገልጿል።
ማህበራዊ
ዩኒቨርሲቲው የአርሶ አደሩን ችግር የሚፈቱ የምርምር ሥራዎችን ሊያጠናክር ይገባል
Jun 23, 2026 22
አሰላ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦የአርሲ ዩኒቨርሲቲ የአርሶ አደሩን ችግር የሚፈቱ የምርምር ሥራዎች ላይ በማተኮር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የአርሲ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሣ (ዶ/ር) አመለከቱ። ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ1 ሺህ 355 በላይ ተማሪዎች ዛሬ አስመረቀ። በወቅቱም የአርሲ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሣ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ተመራቂዎች የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አሻራቸውን ማኖር አለባቸው። ተመራቂዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እየተጓዘች ባለችበት ወቅት መመረቃቸው ብዙ ስራ ይጠብቃቸዋል ብለዋል። ተመራቂዎች የዜጎችን ሕይወት በመቀየር ሂደት ውስጥ የድርሻቸውን መወጣት አለባቸው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ ዩኒቨርሲቲውም የአርሶ አደሩን ችግር በሚፈቱ የምርምር ሥራዎች ላይ በማተኮር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንዲያስቀጥል አመልክተዋል። በተመሳሳይም ጤናን ጨምሮ በማኅበራዊ አገልግሎቶች እያስገኘ ያለውን ውጤታማ የምርምር ሥራዎችና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፍቃዱ ምትኩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ ይገኛል ብለዋል። በግብርና፣ በጤና፣ በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ውጤታማ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማከናወን ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ተማሪዎች ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ የኢንተርፕረነርሺፕ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ አገልግሎትን ለማስፋፋት በሠራው ሥራ የእናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል ገንብቶ ወደ ሥራ ማስገባቱን ገልጸዋል። የአሰላ ሪፈራል ሆስፒታልን ጨምሮ ከወረቀት ንክኪ ነጻ አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤት ማምጣቱንም አክለዋል።
በአምቦ ወረዳ የሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ለአካባቢው ማህበረሰብ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት እየሰጡ ነው
Jun 23, 2026 26
አምቦ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ወረዳ የሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ለአካባቢው ማህበረሰብ በቅርበት አገልግሎት በመስጠት፣ ህብረተሰቡን ከእንግልትና ከተጨማሪ ወጪ እየታደጉ መሆናቸውን ተገልጋዮች ገለጹ። ከወረዳው ነዋሪዎች መካከል አስተያየታቸውን የሰጡት የሀገር ሽማግሌ አቶ ከበደ በየንሳ፤ ቀደም ሲል ህብረተሰቡ የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታትና ፍትህ ለማግኘት ረጅም ርቀት ይጓዝ እንደነበር አስታውሰዋል። ከዚህ ቀደም ፍትህ ለማግኘት ለከፍተኛ ወጪና እንግልት ይዳርጉ እንደነበር ጠቁመው፣ አሁን ላይ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች በአቅራቢያቸው ስራ መጀመራቸው ችግሩን ቀርፎ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት እንዲያገኙ ማገዛቸውን ገልጸዋል። አቶ ከበደ አክለውም፣ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች መቋቋም በተለይም የመደበኛ ፍርድ ቤቶችን መጨናነቅ ከመቀነሱም በላይ፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ጊዜና ገንዘቡን እንዲቆጥብ ትልቅ እገዛ ማድረጉን አስረድተዋል። ሌላኛዋ የወረዳው ነዋሪ ሃደ ሲንቄ እሸቷ ሚደቅሳ በበኩላቸው፤ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ህብረተሰቡን በቅርበት በማገልገልና አለመግባበት ውስጥ የገቡ ወገኖችን በማስማማት ረገድ የሚሰጡት ፍትህ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። አሰራሩ የአካባቢውን ባህልና የገዳ ሥነ-ሥርዓትን መሠረት ያደረገ በመሆኑ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለው ተቀባይነት ከቀን ወደ ቀን እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። የሰደን ሊባን ይግባኝ ሰሚ ባህላዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እና የኦሮሞ አባገዳዎች ኅብረት ሰብሳቢ አባገዳ ወርቅነህ ተሬሳ፤ ፍርድ ቤቱ የአካባቢውን የዳኝነት ባህልና የገዳ ሥነ-ሥርዓት መሠረት በማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት በበጀት ዓመቱ ወደ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቱ ከመጡ መዝገቦች መካከል 96ቱ ውሳኔ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ባህላዊ ፍርድ ቤቶች የሚሰጡት አገልግሎት የማህበረሰቡን ባህላዊ እሴቶች ጠብቆ ለማቆየት እንደሚረዳ፣ ፍትህን በአጭር ጊዜና ያለ ምንም ክፍያ ለማቅረብ ተመራጭ መሆናቸውን አባገዳ ወርቅነህ ተሬሳ አብራርተዋል።
በ 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ለማምጣት ተዘጋጅተናል
Jun 23, 2026 49
ደሴ፤ ሰኔ 16/ 2018 (ኢዜአ)፡-በዘንድሮ ዓመት በሚካሔደው 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅት ማድረጋቸውን በደሴ ከተማ የሚገኙ ተፈታኝ ተማሪዎች ገለፁ። በከተማዋ ከ2 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደሚወስዱ የከተማው ትምህርት መምሪያ አስታውቋል። ተማሪ ቀመርያ ከማል በደሴ ከተማ የሆጤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን፤ በብሔራዊ ፈተናው የላቀ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ለመግባት ዝግጅት ማድረጓን ለኢዜአ ገልፃለች። ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ የነበረውን ትምህርት በመከለስና የተጠናከረ ጥናት በማድረግ የፈተናውን እለት እየተጠባበቀች እንደምትገኝ ነው የምትገልፀው። በትምህርት ቤቱ የመማር ማስተማር ስራው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዞ ጭምር መካሔዱ ለፈተናው በተሻለ ሁኔታ እንድዘጋጅ አድርጎኛል የምትለው ደግሞ ሌላዋ የዚሁ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው ፅዮን ግርማ ነች ። "ጊዜዬን በአግባቡ በመጠቀም በትጋት እየተዘጋጀሁ ነው" ያለችው ጽዮን ፈተናውን ተረጋግቶ በመስራት ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት ትኩረት ሰጥቼ እየተዘጋጀሁ ነው ብላለች። የመምህር አካለ ወልድ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሰሚራ ክንዱ ፤በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናው የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተወዳዳሪ ለመሆን በቂ ዝግጅት ማድረጓን ነው የገለፀችው ። የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ የምትፈልገው ቦታ ላይ ለመድረስ የራስ ጥረት ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ ሌት ተቀን ጥረት እያደረገች መሆኑዋንም ነው የምትናገረው። የሆጤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ጌታቸው መከተ በበኩላቸው፣ በዘንድሮውዓመት ትምህርት ቤቱ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ላይ የሚያስቀምጣቸው ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል ነው ያሉት። ለተፈታኞች ቤተ መጽሕፍቶችና ቤተ ሙከራዎችን የስራ ሰዓታቸውን ጭምር ከማራዘም ባለፈ የማካካሻ ትምህርትን በመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፍቅር አበበ በበኩላቸው፣ በከተማው 2 ሺህ 854 ተማሪዎችን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደሚወስዱ ገልፀዋል። ተማሪዎቹ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡም ቅድመ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱንም ነው የገለጹት፡፡
ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes)
Jun 23, 2026 220
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው · ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ሕጻናት ላይ የትኛው የስኳር ህመም ነው በስፋት እየተከሰተ ያለው? በሕጻናት ላይ የሚከሰቱ የተለያዩ የስኳር ህመም ዓይነቶች መኖራቸውን የሚገልጹት የሕጻናት የስኳር ህመም ስፔሻሊስት ዶክተር ሰውአገኝ የሺዋስ፤ እንደሀገራችን ግን በዋናነት የሚጠቀሰው ዓይነት አንድ የሚባለው የስኳር ህመም ነው ይላሉ። በአደጉ ሀገራት ላይ ዓይነት ሁለት የስኳር ህመምም በሕጻናት ላይ እንደሚከሰት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም ባብዛኛው እንቅስቃሴ ካለማድረግ፣ ከኑሮ ዘይቤ እንዲሁም ከመጠን ባለፈ ውፍረትና ተያያዥ ጉዳዮች ምክንያት የሚከሰት መሆኑንም ያስረዳሉ። ይሁን እንጅ በእኛ ሀገር ደረጃ ይህ (ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም) በስፋት በሕጻናት ላይ እንደማይስተዋልና ብዙም አሳሳቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። በዋናነት በእኛ ሀገር ሕጻናት ላይ እየተከሰተ ያለው ዓይነት አንድ የስኳር ህመም መሆኑን ገልጸው፤ተገቢው ጥንቃቄ ባለመደረጉ ልጆች ለውስብስብ ችግር እየተዳረጉ ነው ብለዋል። እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የጡት ካንሰርን ለመከላከል ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? · ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም አጋላጭ ምክንያቱ ይታወቃል? እንደ ባለሙያው ገላጸ፤ ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም አጋላጭ መንስዔው አይታወቅም። ይህን ተከትሎም አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል ሕክምና የለም። እንደ አጋላጭ ከሚታሰቡት መከካል ግን፤ ልጆች በተፈጥሮ ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም የመጋለጥ ዕድላቸው ከፍተኛ መሆኑ እና ውጫው (አካባቢያዊ ሁኔታዎች) በምክንያትነት ይነሳሉ ብለዋል። በእነዚህ ምክንያቶች በእያንዳንዱ የሰውነት እንቅስቃሴ ውስጥ ስኳር እንዲዋሃድ የሚያደርገው ኢንሱሊን የተሰኘ ሆርሞን መመረቱ ይቆማል፤ የኢንሱሊን እጥረት ሲያጋጥም ደግሞ ስኳር ደም ላይ እየጨመረ ይሄዳል፤ ደም ከ180 በላይ ከፍ በጊዜም ኩላሊት ወደ ውጭ ያስወግደዋል፤ በዚሁ ወቅትም ጠቃሚ ንጥረ ቅመሞች ጭምር ከሰውነት ይወገዳሉ፤ የፈሳሽ እጥረትም ያጋጥማቸዋል፤ ከዚያም የልጆች የሰውነት ክብደት መቀነስና ቶሎ ቶሎ (ከመደበኛው የተለየ) የመሽናት ሁኔታ ይከሰታል ሲሉ አብራርተዋል። · ዓይነት አንድና ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም እንደ ዶክተር ሰዋገኝ ማብራሪያ፤ ዓይነት አንድ እና ዓይነት ሁለት የስኳር ህመሞች የተለያዩ ናቸው። ዓይነት አንድ የስኳር ህመም ማለት፤ ኢንሱሊን በሰውነት ውስጥ ሳይመነጭ ሲቀር የሚከሰት መሆኑን አስረድተዋል። ይህን ህመም ቀድሞ መከላከል አይቻልም፤ ሲከሰት ሕክምና ማግኘት እንጅ ይላሉ። ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም፤ ኢንሱሊን የማመንጨት ችግር ሳይሆን፤ ኢንሱሊኑ በሰውነት ውስጥ ሳይሠራ ሲቀር የሚከሰት ነው ይላሉ። ይህም ከሰውነት ክብደት መጨመር፣ አካላዊ እንቅስቃሴ ባለማድረግ ምክንያት የሚመጣ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲውም ብዙ ጊዜ በዐዋቂዎች ዘንድ በስፋት የሚስተዋል ህመም መሆኑንም አመላክተዋል። ይህን ህመም አመጋገብን በማስተካከል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ፣ የኑሮ ዘይቤን በማስተከከል ቀድሞ መከላከል እንደሚቻልም ነው ያስገነዘቡት። · የስኳር ህመም በየትኛው የዕድሜ ክልል ይከሰታል? ዓይነት አንድ የስኳር ህመም የ6 ወር ዕድሜ ካለው ሕጻን ጀምሮ እስከ በዐዋቂነት የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ዶክተር ሰውአገኝ ይናገራሉ። ይህን ሲያብራሩም በተለይም ከ30 ዓመት በታች ባሉት የዕድሜ ክልሎች (በተለይም ከ5 - 7 እንዲሁም ከ14 - 15 ዓመት) ባሉ ልጆች ላይ በስፋት ከሰታል ብለዋል። · ምልክቶቹ በውል ይታወቃሉ? በአብዛኛው ከተለመዱ ምልክቶች መካከል፤ ቶሎ ቶሎ ውኃ መጠጣት፣ የማይረካ የውኃ ጥማት መኖር፣ ከወትሮው የተለየ ሌሊትን ጨምሮ ሽንት የመሽናት፣ ክብደት መቀነስ የሚሉት እንደሚገኙበት ይገልጻሉ። እነዚህ ምልክቶች ሲታዩም ጊዜ ሳያባክኑ (ህመሙ ሥር ሳይሰድ) ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ ተገቢ መሆኑን መክረዋል። በዚህ ሂደት ልጆች ህመማቸውን ዐውቀውና ራሳቸውን ችለው ወደ ሕክምና ተቋም እንደማይሄዱ ስለሚታወቅ ወላጆች (አሳዲዎች) ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ሾተላይን ቀድሞ መከላከል ይቻላል? · ሕክምና እና ምክረ ሐሳብ ምንም እንኳ አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል የታወቀ ነገር ባይኖርም ዓይነት አንድ የስኳር ህመም፤ ቶሎ ከታወቀና ሕክምና ከተደረገለት ልጆች እንደማንኛውም ጤናማ ልጅ ዕድገታቸው ይቀጥላል፣ ትምህርታቸውን መማር፣ ኑሯቸውን መቀጠል ይችላሉ። ልጆች በጊዜው (ህመሙ እንደተከሰተ ወዲያውኑ) ካልታከሙ ሕይዎታቸውን እስከማጣት የሚደርስ ውስብስብ ችግር የሚፈጥር መሆኑን ገልጸው፤ ወላጆች (አሳዳጊዎች) የልጆቻቸውን ጤና በአግባቡ እንዲከታተሉ መክረዋል።የተለየ ምልክት ሲያስተውሉም ወደ ሕክምና መሄድን መክረዋል። ምንም እንኳን አመጋገብን ማስተካከል ለጤና እንደ ግብዓት ተጠቃሚ መሆኑ ቢታመንም፤ ዓይነት አንድ የስኳር ህመምን በአመጋገብ ብቻ እናስተካክላለን በሚል መዘናጋት ተገቢ እንዳልሆነ ሕብረተሰቡ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል። በአመጋገብ ብቻ እናስተካክላለን ማለት ቶሎ እንዳይታከሙ ጊዜ በማባከን የልጆችን ጤና በይበልጥ ማወሳሰብ በመሆኑ፤ አዋጩ መፍትሔ በሕክምና ኢንሱሊን መስጠት እና በተጨማሪ አመጋገብን ከኢንሱሊኑ ጋር ማጣጣም መሆኑን አስገንዝበዋል። #የጤና_ነገር #ኢዜአ #ኢንሱሊን #የስኳር_ህመም #ሕጻናት
ኢኮኖሚ
ዘላቂ ለውጥ የሚመጣው በጋራ በመቆም ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jun 23, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018(ኢዜአ) ፦ ሀገርን መገንባት በአንድ ትውልድ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን የሁላችንም የጋራና ቀጣይነት ያለው ሥራ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” የተሰኘ ብሔራዊ ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሔደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” በተሰኘው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በመገኘቴ ታላቅ ክብር ይሰማኛል ሲሉ ገልጸዋል። “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ፣ በየደረጃው የተጓዝንበትንና አሁን የደረስንበትን መንገድ መለስ ብዬ እንድቃኘው አድርጎኛል ሲሉም ገልጸዋል። ሀገራችን በራሷ አቅም ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመገንባት፣ ያልተሞከሩ ግዙፍ ልማቶችን በማከናወን በየጊዜው ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረች ትገኛለች ብለዋል። እነዚህ ሁሉ በአጋጣሚ የተገኙ ድሎች አይደሉም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመደመር መንፈስ ላይ ተመስርተው፣ ዘላቂ ለውጥ የሚመጣው በጋራ በመቆም ነው በሚል ጽኑ እምነት የተወሰዱ በቆራጥ ውሳኔዎች የተገኙ ውጤቶች ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም የጀመርናቸው ለውጦች በራሳቸው የመጨረሻ ግብ አይደሉም ይልቁንም ከእኛ በኋላ ለሚመጡት ተከታታይ ትውልዶች የምንጥለው ጠንካራ መሠረት ነው ብለዋል። ሀገርን መገንባት በአንድ ትውልድ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን የሁላችንም የጋራና ቀጣይነት ያለው ሥራ በመሆኑ፤ በዚህ ጽኑ እምነት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይህንን መንፈስ ይዞ ወደፊት እንዲጓዝ፣ የተቀበለውን ወረት አግዝፎ ይበልጥ ወደ ላቀ ከፍታ እንዲያመራ ጥሪዬን አቀርባለሁ ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭን በመደመር መንግስት እይታ በፍጥነትና በጥራት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው -ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ
Jun 23, 2026 154
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018(ኢዜአ) ፦ በሀረር ከተማ የተጀመረው ሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭ በመደመር መንግስት እይታ ጥራትና ፍጥነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ በሀረር ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን የሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በመስክ ምልከታው ላይም ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለፁት በአው ሀኪም ተራራ ላይ እየተሰራ የሚገኘው ኢኒሼቲቩ የአዲሲቷ ሀረር አለም አቀፍ ምልክት ከመሆን ባሻገር ለክልሉ የቱሪዝም ዘርፍ እድገት ጉልህ ፋይዳ ያበረክታል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም ለቱሪዝም መዳረሻነትና ለህዝብ መዝናኛነት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የፕሮጀክቱ እውን መሆን የጎብኚዎችን ቆይታ በመጨመር ተጠቃሚነትን ከማሳደግ አንፃርም ሚናው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል። በፕሮጀክቱም 1ሺህ 870 ደረጃዎች እንደሚኖሩት እና ሁለት ኪሎ ሜትር የሚጠጋ የመሰረተ ልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ አካባቢያዊ ሀብቶችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ተራራው ራሱን የቻለ የህግ ማዕቀፍ እንዲኖረው በማድረግ ተገቢው ጥበቃ እንደሚደረግለት አመላክተው ለዚህም ህገ-ወጥ ግንባታ በመከላከል ረገድ በቅንጅት እንደሚሰራም ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ተራራውን አረንጓዴ የማልበስ ስራ ይሰራል ብለዋል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመው ለዚህም የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉ ነው የተናገሩት።
በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተሞች የኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥረዋል
Jun 23, 2026 123
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተሞች የኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ እድል መፍጠራቸውን የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊዎች ገለጹ፡፡ በአዲስ አበባ ተጀምሮ የከተማ ገጽታን በመቀየርና የነዋሪዎችን ህይወት በማዘመን ረገድ አንጸባራቂ ውጤት የተመዘገበበት የኮሪደር ልማት አሁን ላይ ወደ ክልል ከተሞች ተስፋፍቶ ቀጥሏል፡፡ በአዲስ አበባ እንደታየው ሁሉ በክልል ከተሞች የተሽከርካሪና የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መስመሮች፣ የንግድና የሕዝብ መዝናኛ ሥፍራዎች ደረጃቸውን ጠብቀው ተገንብተዋል፡፡ ይህም ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድልን የፈጠረው የልማት ሥራ የከተሞችን ውበት እና ለኑሮ ያላቸውን ምቾት በእጅጉ እየጨመረው ይገኛል። የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተሞች የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለወጣቱ ሰፊና ዘላቂ የሥራ እድል መፍጠር ችለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራ እና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አስፋው ለገሰ፤ ኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሜጋ ፕሮጀክቶች በርካታ ዜጎችን በሥራ ዕድልና በንግድ ሥራ ተጠቃሚ ማድረጋቸውን አንስተዋል። በከተማዋ በተከናወኑ የወንዝ ዳርቻ ልማት፣ የፓርኮች ግንባታ እና የቤት ልማት ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ቁጥር ላላቸው ወጣቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡ ቢሮው በ2018 በጀት ዓመት እስካሁን ድረስ ከ365 ሺህ በላይ ዜጎች በተለያዩ መስኮች ወደ ሥራ መሰማራታቸውን ተናግረዋል፡፡ በከተማዋ ኢንዱስትሪ፣ ኮንስትራክሽን፣ የከተማ ግብርና፣ አገልግሎት በስፋት የሥራ ዕድል የተፈጠረባቸው የሥራ መስኮች መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፣ ከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ እስካሁን ለ19 ሺህ 642 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም በከተማዋ የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ጉልህ ድርሻ ማበርከታቸውን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያን የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብቶች ምርታማነት የማሳደግ የዝርያ ማሻሻል ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
Jun 22, 2026 776
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ):- የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ዝርያን የሚያሻሽሉ ሙያተኞችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል። በዚህም ኢንስቲትዩቱ ከሰኔ 08 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በሰው ሰራሽ ማዳቀል የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ዝርያን ለማሻሻል ለሙያተኞች የሰጠውን ስልጠና በማጠናቀቅ ሰልጣኞችን አስመርቋል። የግብርና ሚንስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ፤ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ያላት ሀገር ናት ብለዋል። የኢትዮጵያን የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ለማሻሻልም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችንና የአሰራር ሥርዓቶችን በመቅረፅ እየተሰራባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ለማሻሻል እየተሰራበት የሚገኘው የሰው ሰራሽ ማዳቀል ሥነ-ዘዴ ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩትም የሰው ሰራሽ ማዳቀል ሙያተኞችን በብዛትና በጥራት ለማፍራት መሰረት መጣሉን አንስተዋል። በኢንስቲትዩቱ ትምህርትና ስልጠና የተሰጣቸው ሙያተኞችም የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን በማሻሻል ህዝባቸውን ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የመደመር መንግሥት የገጠር ሽግግርን ለማሳለጥ ለእንስሳት ሃብት ምርታማነት ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸዋል። በዚህም የመንግሥትን መርህ ታሳቢ በማድረግ በሰው ሰራሽ የማዳቀል ሥነ-ዘዴ የፍየልና በግ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትና ጤንነት ሙያተኞችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ለምርቃት ለበቁት ሰልጣኝ ሙያተኞችም በእንስሳት እንክብካቤና አመጋገብ፣ በሽታ መከላከልና ጤና አጠባበቅ፣ ምርት ማቀነባበሪያና የገበያ ትስስር ትምህርት መሰጠቱን አስረድተዋል። በስልጠናውም የያቤሎ፣ ጂንካ፣ ባኮ፣ አዳሚቱሉ፣ የዓርባ ምንጭ ምርምር ማዕከላት፣ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት እንዲሁም የግል እርሻ ሙያተኞች መሳተፋቸውን አስረድተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ
Jun 22, 2026 517
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) የፌዴሬሽኑን አሰራርና መረጃ አያያዝ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመንና በጋራ ለመስራት የሚያስችል የፕሮጀክት ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ፌደሬሽኑ ዘመናዊ የምዝገባ ሥርዓትን በመዘርጋትና ተቋሙን ዲጂታላይዝ በማድረግ ረገድ ብዙ መሥራት እንደሚገባ አመልክተዋል። በስምምነቱ መሰረት በቴክኖሎጂ የዳበረ ተቋም ለመገንባት ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) በትብብር እንደሚሰራ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ፈጣንና ቀልጣፋ የአትሌቶች አገልግሎት ለመስጠት በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) የኢንፎርሜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃኒባል ለማ፤ አትሌቲክስ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ያኮራ ታላቅ ዘርፍ መሆኑን ገልጸዋል። የፌዴሬሽኑ የዲጂታል ሉዓላዊነት (Digital Sovereignty ) ለማጠናከር ፣ ከዓለም አትሌቲክስ ጋር ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖረው የሚያስችል የቴክኖሎጂ ትስስርን ጨምሮ አስፈላጊው ሁሉ ለማድረግ ተቋማቸው ለአትሌቲክሱ እድገት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ስምምነቱ ከስልጠና ማዕከላት ጀምሮ ፕሮጀክቶችን፣ ክለቦችን እና ተቋማትን ያቀፈ የአትሌቶች ምዝገባ ሥርዓትን የሚዘረጋ ሲሆን፤ የውድድሮችን የአደረጃጀትና የአመራር (ማኔጅመንት) ሥርዓት ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። ከአትሌቶች አገልግሎት ጋር የተያያዙ የኤምባሲ ጉዳዮችን ከእጅ-በእጅ (ማኑዋል) አሰራር ወደ ዲጂታል ሥርዓት የሚቀይር በመሆኑ፣ ይደርስ የነበረውን እንግልት እንደሚያስቀርም ፌዴሬሽኑ ገልጿል። በተጨማሪም ስምምነቱ የፋይናንስ፣ የንብረት አስተዳደር እና የግዥ ሥርዓቶችን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የሚያስችል ሲሆን፤ የፌዴሬሽኑን ድረ-ገጽ (ዌብሳይት) ማበልጸግን ጨምሮ በርካታ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎችን የሚያካትት ነው።
ዩኒቨርሲቲው የቱሪዝም ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ያጠናክራል
Jun 22, 2026 439
ሮቤ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝም ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን እንደሚያጠናክር ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው "የቱሪዝምና መስተንግዶ ትምህርትን በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ማዕቀፍ መቃኘት" በሚል መሪ ሐሳብ 2ኛውን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ኮንፈረንስ ማካሄድ ጀምሯል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እና የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፤ በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፉን በማልማት ዓለም አቀፍ ተመራጭነቷን ለማስፋት በምታደርገው ጥረት ቴክኖሎጂ ዋና ግብዓት ነው ብለዋል። በዚህም የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ከዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ጋር በማስተሳሰር ወደ ሥራ መገባቱንም አንስተዋል። ይህም በቱሪዝም ዘርፉ የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል ልማት በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የራሱ ድርሻ እንዳለው ጠቁመዋል። መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የባሌና አካባቢውን የቱሪዝም እምቅ አቅም ለማልማት የሚደረገውን ጥረት በምርምርና በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እንዲደገፍ ለማድረግ መሥራቱ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል። የአሁኑ የምርምር ኮንፈረንስ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ኢኒሼቲቭ ለማሳካት መሠረት እንደሚጥል ተናግረዋል። ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈው ይህ የምርምር መድረክ፤ ዩኒቨርሲቲው በቱሪዝም ዘርፍ የጀመረውን የማስተዋወቅ፤ የማነቃቃትና የምርምር ሥራዎች ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ተጨማሪ አቅም እንደሚሆንም አክለዋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን የቱሪዝም እምቅ አቅም ለማልማት የሚደረገውን ጥረት በምርምር እያገዘ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለዚህም በባሌና በምሥራቅ ባሌ አካባቢ የሚገኙ በርካታ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ የቱሪስት መስህቦችን በሳይንሳዊ መንገድ የማጥናት፤ የማስተዋወቅና እንዲለሙ በቅንጅት የመሥራት ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለአብነትም የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክና የድሬ ሼህ ሁሴን የመስህብ ስፍራዎች እንዲለሙና እንዲተዋወቁ ዩኒቨርሲቲው የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አመልክተዋል። ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀው ይህ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስም የቱሪስት መስህቦችን ለማልማትና ለማስተዋወቅ እያደረገ ላለው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፤ የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ በቱሪስት መዳረሻዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ብለዋል። ለዚህም የሰው ኃይል ልማትን ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር ባለሙያዎች በዕውቀትና በክህሎት ብቁ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለተግባራዊነቱም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የቱሪዝምና የሆቴል ኢንዱስትሪውን የሚመጥን ብቁ ባለሙያ የማፍራት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፤ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ እያደረጋቸው ያሉ የምርምር ሥራዎች ለዚህ ጥረት ትልቅ አጋዥ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከኮንፈረንሱ መክፈቻ ጎን ለጎንም መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK) የመጡ የባለሙያዎች ቡድን ጋር በቅርብ ትብብር ያበለጸገውንና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀውን አዲሱን የዩኒቨርሲቲውን ድረ-ገጽ በይፋ አስመርቋል።
የሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም አስተማማኝ የሃይል አቅርቦት እንዲፈጠር እየተደረገ ነው
Jun 22, 2026 394
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦የሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም አስተማማኝ የሃይል አቅርቦት እንዲፈጠር እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ገለጹ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ለኢዜአ እንዳሉት፤ አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት መስመሮችንና የዲስትሪቡዩሽን ትራንስፎርመሮችን ብቃት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው። የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግርን ለመፍታት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማትን የማሻሻል፣ መልሶ የማቋቋምና የቅድመ-መከላከል ጥገና ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። ድንገተኛ ብልሽቶችን አስቀድሞ ለመለየትና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመዘርጋትም ዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ጥቅም ላይ እየዋሉ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ አገልግሎት፣ ከመንግሥትና የልማት አጋሮች የሚመነጭ የገንዘብ ሃብትን በመጠቀም መሰረተ ልማት የማሻሻል ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ከመሠረተ ልማት ግንባታው ጎን ለጎንም የደንበኞችን አገልግሎት ጥራትና ፍጥነት ማሻሻል የሚያስችሉ ሰፋፊ የትራንስፎርሜሽን ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን በመተግበር የኔትወርክ አቅምን የማሳደግ፣ መልሶ የማደራጀትና የቅድመ-መከላከል ጥገና ሥራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። ደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻልም የውስጥ አቅምን የማጠናከርና የጥገና ቡድኖችን በአዲስ መልክ የማደራጀት ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የተፈጠረው ውጤታማ የደንበኞች አገልግሎትም ውጤታማነትን እያሻሻለ መሆኑን አስረድተዋል።
ኢንስቲትዩቱ የፍትህ ዘርፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 20, 2026 1116
አዳማ፣ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ሕግ ምርምርና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የፍትህ ዘርፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ። ኢንስቲትዩቱ የፍትህ ሪፎርሙን ለማሳካት ያካሄዳቸውን የምርምር ውጤቶች በግብዓት ለማዳበር የሚያስችል የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አባገዳ አዳራሽ በማካሄድ ላይ ይገኛል። የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት አቶ ገዛሊ አባ ሲመል ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት በጥናትና ምርምር የተደገፉ የመፍትሔ ሐሳቦችን እያቀረበ ይገኛል። በመድረኩ ላይ በቁልፍ የፍትህ ዘርፍ ጉዳዮች ዙሪያ የተከናወኑ አምስት የተለያዩ የምርምር ውጤቶች እንደሚቀርቡ ተናግረዋል። ምርምሮቹም የፍትህ አካላት ስነ-ምግባር፣ የፌዴራልና የክልል የህግ ተፈፃሚነት ወሰን ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶች፣ በፍትህ ዘርፉ የዲጂታል አገልግሎት ዘመን የቋሚና ተዘዋዋሪ ችሎት አስፈላጊነት፣ እንዲሁም የህግ ትርጓሜና የተፈፃሚነት ወሰን የተመለከቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህ የምርምር ውጤቶች ጠንካራ የፍትህ ስርዓት በመገንባት በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የፍትህ ዘርፍ ሪፎርም ለማሳካት ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተለይም በህግና በአሰራር ዙሪያ ያሉትን ክፍተቶች ለመድፈን በእጅጉ ያግዛሉ ብለዋል። የኦሮሚያ ህግ ምርምርና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ አዱኛ ሙሐመድ በበኩላቸው፤ ኢንስቲትዩቱ በክልሉ የፍትህ ስርዓትን ለማሻሻል እስካሁን ከ100 በላይ የምርምር ስራዎችን በማካሄድ በግብዓትነት እንዲያገለግሉ ማድረጉን ጠቁመዋል። በተለይም በዘርፉ የተጀመሩ የሪፎርምና የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ስራዎችን ለማሳለጥ በጥናትና ምርምር ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ የፍትህ ስርዓቱን አሰራር ለማዘመንና በቴክኖሎጂ ለመምራት የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ለዛሬው መድረክ መቅረባቸውን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ ከጥናትና ምርምር ስራዎች ጎን ለጎን፣ ብቁ የፍትህ አካላትን ለማፍራትና ጥራትን ለማረጋገጥ ለህግ ባለሙያዎች የስልጠናና የአቅም ግንባታ ስራዎችን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝም ዋና ዳይሬክተሯ አክለዋል። በመድረኩ ላይ በፌዴራልና በክልል የሕግ ወሰን ተፈጻሚነት ዙሪያ የተካሄደውን ምርምር ያቀረቡት አብዲሳ ጉርሜ (ዶ/ር)፤ የጥናቱ ውጤት በፌዴራልና በክልል የሕግ ተፈጻሚነት ረገድ የሚታዩ ውስንነቶችን በግልጽ በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከቱን አስገንዝበዋል። በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ከኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እና ከፌዴራል ፍትህ ኢንስቲትዩት የተጋበዙ ተመራማሪዎችና የህግ ምሁራን በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ስፖርት
ጋና ከእንግሊዝ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከኮሎምቢያ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Jun 23, 2026 147
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የ12ኛ ቀን ውሎ የምድብ 11 እና 12 ሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። በምድብ 12 እንግሊዝ ከጋና ምሽት አምስት ሰዓት ላይ በቦስተን ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ እንግሊዝ ክሮሺያን 4 ለ 2፣ ጋና ፓናማን 1 ለ 0 አሸንፈዋል። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። እ.አ.አ በ2011 በዌምብሌይ ስታዲየም ባደረጉት የወዳጅነት ጨዋታ አንድ አቻ የተለያዩበት ውጤት ብቸኛ የእርስ በእርስ ግንኙነታቸው ነው። በዛሬው ጨዋታ እንግሊዝ የማሸነፍ የቅድሚያ ግምቱን ብትወስድም ጋና ጠንካራ ፉክክር ታደርጋለች ተብሎ ይጠበቃል። አሸናፊው ሀገር ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ያረጋግጣል። በዚሁ ምድብ ሌላኛው መርሐ ግብር ፓናማ ከክሮሺያ በቶርንቶ ስታዲየም ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸው ሽንፈት ያስተናገዱት ሁለቱ ሀገራት በውድድሩ ላይ ለመቆየት ከዛሬው ጨዋታ ሶስት ነጥብ መውሰድ ይጠበቅባቸዋል። በምድብ 11 ኮሎምቢያ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከሌሊቱ 11 ሰዓት በጓድላሃራ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኮሎምቢያ ኡዝቤኪስታንን 3 ለ 1 በመርታት ዓለም ዋንጫውን በድል የጀመረች ሲሆን ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከፖርቹጋል አንድ አቻ ተለያይታለች። ከ52 ዓመታት በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫው የተመለሰችው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመጀመሪያ ዓለም ዋንጫ ጎሏን በአሮን ዊሳ አማካኝነት አግኝታለች። በውድድሩ የመጀመሪያ ነጥቧን አስመዝግባለች። የማዕከላዊ አፍሪካ ሀገር ወደ ጥሎ ማለፉ የመግባት እድሏን የዛሬውን ጨዋታ በድል መወጣት ይኖርባታል። ሁለቱ ሀገራት እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። በዚሁ ምድብ ፖርቹጋል ከኡዝቤኪስታን ጋር ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በሂውስተን ስታዲየም ጨዋታዋን ታከናውናለች። ፖርቹጋል ከመጀመሪያው ጨዋታ የአቻ ውጤት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ትፋለማለች። የማሸነፍ ሰፊ የቅድሚያ ግምትም አግኝታለች። በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን እያደረገች የምትገኘው ኡዝቤኪስታን ከሽንፈት አገግማ ድል የማስመዝገብ ከባድ የቤት ስራ ይጠብቃታል።
አልጄሪያ በዓለም ዋንጫው የመጀመሪያ ድሏን አስመዘገበች
Jun 23, 2026 147
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ አልጄሪያ ከመመራት ተነስታ ጆርዳንን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ማለዳ ላይ በሳን ፍራንሲስኮ ቤይ ኤሪያ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ 10 ጨዋታ ኒዛር አል ራሽዳን በ36ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ጆርዳን መሪ ሆናለች። ከእረፍት መልስ ናዲር ቤንቡአሊ በ69ኛው ደቂቃ አልጄሪያን አቻ ያደረገችውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። አሚን ጎሪ በ82ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ግብ አልጄሪያን ድል እንድትቀዳች አስችሏል። የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር የጨዋታ የበላይነት ነበራት። በውድድሩ የመጀመሪያ ድሏን ያስመዘገበችው አልጄሪያ በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዛለች። ወደ ጥሎ ማለፉ የመግባት እድሏን አስፍታለች። ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ጆርዳን ከዓለም ዋንጫው ተሰናብታለች። ጆርዳን በዓለም ዋንጫው ስትሳተፍ የዘንድሮው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። በዚሁ ምድብ ትናንት ማምሻውን በተደረገ ጨዋታ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ አርጀንቲና ኦስትሪያን 2 ለ 0 በመርታት ወደ ጥሎ ማለፉ ተሸጋግራለች። አልጄሪያ ከኦስትሪያ፣ ጆርዳን ከአርጀንቲና በምድብ 10 የሚደረጉ የመጨረሻ ጨዋታዎች ናቸው።
ፈረንሳይ እና ኖርዌይ ጥሎ ማለፉን መቀላቀላቸውን አረጋገጡ
Jun 23, 2026 181
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የምድብ ዘጠኝ ሁለተኛ ጨዋታዎች ከእኩለ ሌሊት በኋላ ተደርገዋል። በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኖርዌይ ሴኔጋልን 3 ለ 2 አሸንፋለች። አርሊንግ ሃላንድ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ማርከስ ሆልምግሬን ፔደርሰን ቀሪዋን ጎል ለኖርውይ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ኢስማኤላ ሳር ለሴኔጋል ግቦቹን አስቆጥሯል። በጨዋታው ሴኔጋል የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ብትወስድም ኖርዌይ የግብ እድሎችን በመፍጠር ተሽላ ተገኝታለች። በመጀመሪያ የዓለም ዋንጫው እየተሳተፋ የሚገኘው አርሊንግ ሃላንድ በውድድሱ ላይ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት አራት አድርሷል። ሃላንድ የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። ውጤቱን ተከትሎ ኖርዌይ ወደ ጥሎ ማለፍ (32 ውስጥ) አልፋለች። በውድድሩ ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ሴኔጋል በሂሳባዊ ስሌት ወደ ጥሎ ማለፉ ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ መግባት በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢራቅን ማሸነፍ ይጠበቅባታል። በዚሁ ምድብ በፊላደልፊያ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፈረንሳይ ኢራቅን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ኪሊያን ምባፔ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኡስማን ደምቤሌ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ምባፔ በዓለም ዋንጫው በአጠቃላይ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 16 በማድረስ ከጀርመኑ ሚሮስላቭ ክሎዝ (16) እኩል በመሆን ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። 18 ግቦች ካስቆጠረው የአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ በሁለት ጎል ዝቅ ብሎ ይገኛል። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛትም አራት አድርሷል። ምባፔ ለፈረንሳይ 100ኛ ጨዋታውን ያደረገ ሲሆን 59 ግቦችን በማስቆጠር የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን አጠናክሯል። የጨዋታው ኮከብ በመባል ተመርጧል። በመብረቅ እና በመጥፎ የአየር ንብረት ምክንያት ለሁለት ሰዓት ከ15 ደቂቃ ተቋርጦ በነበረው ጨዋታ ፊረንሳይ ብልጫ ወስዳ ተጫውታለች። ውጤቱን ተከትሎ ፈረንሳይ በስድስት ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብታለች። በምድቡ ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ኢራቅ ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ የማለፍ እድሏን ለመጠቀም ሴኔጋልን በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ማሸነፍ ይጠበቅባታል። ፈረንሳይ ከኖርዌይ፣ ሴኔጋል ከኢራቅ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ናቸው።
ሜሲ የዓለም ዋንጫን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረ ወሰን በሰበረበት ጨዋታ አርጀንቲና ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች
Jun 22, 2026 636
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የምድብ 10 መርሐ ግብር አርጀንቲና ኦስትሪያን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በዳላስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሊዮኔል ሜሲ በ38ኛው እና በ95ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥሯል። ሜሲ በዓለም ዋንጫው ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 18 በማድረስ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን ክብረ ወሰን ከጀርመኑ ሚሮስላቭ ክሎዝ (16 ጎል) ተረክቧል። ሜሲ በስምንተኛው ደቂቃ ቡድኑ ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ስቷል። የ38 ዓመቱ ተጫዋች በአጠቃላይ ለሀገሩ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 122 በማድረስ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን አጠናክሯል። ውጤቱን ተከትሎ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ አርጀንቲና በስድስት ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፍ ገብታለች። ኦስትሪያ በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዚሁ ምድብ ጆርዳን ከአልጄሪያ በሳንፍራንሲስኮ ቤይ ኤሪያ ስታዲየም ከማለዳው 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሁለቱ ሀገራት በመጀመሪያ ጨዋታቸው ሽንፈት አስተናግደዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በምዕራብ ወለጋ ዞን ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ67 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ዝግጁ ሆኗል
Jun 23, 2026 90
ጊምቢ፣ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ67 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ዝግጁ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ፤ በዞኑ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኞችም ሆነ የመሬት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በበጋ ወቅት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማቶችን ጨምሮ በተመረጡ ከ67 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ችግኞች ይተከላሉ ብለዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች ተመናምኖ የነበረውን የደን ሽፋን ከመመለሱ በላይ፣ ለብዝሃ ሕይወት ምቹ አካባቢ መፍጠር ማስቻሉን ተናግረዋል። በተለይም የመሬት ለምነትን ጠብቆ በማቆየትና የቡናና የሰብል ምርት መጠንን በማሻሻል የተራቆቱ አካባቢዎች ዳግም ወደ ለምነታቸው እየተመለሱ ነው ብለዋል። እንዲሁም ለእንስሳት እርባታ፣ ለንብ ማነብ፣ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምቹ ሥነ-ምህዳር ከመፍጠርም ባለፈ በርካታ ወገኖችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከማድረግ ረገድ አበርክቶው የጎላ እንደነበረ ገልጸዋል። የዞኑ አርሶ አደሮች ባዩት ለውጥ በመነሳሳት በየዓመቱ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በስፋት የማዘጋጀት ባህል ከማዳበር ባሻገር ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ እያስቻላቸው መሆኑንም አብራርተዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች ከ328 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መጠናቀቁን አቶ ፍቅሩ ጠቁመዋል። ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል አቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ብርቱካን፣ አፕልና ለሌሎች የደን ሽፋን የሚውሉ በርካታ ችግኞች መዘጋጀታቸውን አንስተዋል። የችግኝ ማፍላት ሥራው በመንግሥት፣ በግል እና በማህበራት አማካኝነት መካሄዱን አንስተዋል። ሕብረተሰቡን በማሳተፍ ለተከላው 293 ሚሊዮን ጉድጓድ መዘጋጀቱንና፤ ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን በማሳተፍ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የመዲናዋ ነዋሪ ኃላፊነቱን በመወጣት አካባቢውን ከጎርፍ አደጋ ሊጠብቅ ይገባል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 23, 2026 159
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፡- የከተማችን ነዋሪዎች የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮችን በማፅዳትና ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ አካባቢያችሁን ከጎርፍ አደጋ ልትጠብቁ ይገባል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጥሪ አቀረቡ። ከንቲባ አዳነች በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአቃቂ ቃሊቲ ብዙ ጊዜ ለጎርፍ ተጋላጭ በሆነው ቦታ ላይ ጎርፍን የመከላከልና የአደጋ ዝግጁነት ሥራን በይፋ አስጀምረናል ብለዋል። አቃቂ ቃሊቲ በተፈጥሯዊ አቀማመጡ የአዲስ አበባ የታችኛው ክፍል በመሆኑ፤ ከዚህ በፊት በጎርፍ አደጋ በተደጋጋሚ ተጠቂ ሲሆን መቆየቱንም አውስተዋል። በዛሬው ዕለትም ለዚህ አካባቢ ቅድሚያ በመስጠት በሁሉም የከተማችን ቦታዎች ላይ ወንዞች ተፈጥሯዊ ፍሰታቸውን ጠብቀው እንዲፈስሱ የተለያዩ ግንባታዎችን የመሥራትና የፍሳሽ መስመሮችን የማፅዳት ንቅናቄን አስቀጥለናል ሲሉም አስታውቀዋል። ውድ የከተማችን ነዋሪዎችም አሥተዳደራችን እየሠራ ባለው የመከላከልና አደጋ እንዳያጋጥም የቅድመ ዝግጁት ሥራ ላይ በንቃት ተሳተፉ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። አክለውም፤ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮችን በማፅዳትና ቆሻሻን ወደ ፍሳሽ መውረጃ ባለመጣልና በአግባቡ በማስወገድ አካባቢያችሁን ከጎርፍ አደጋ ጠብቁ ሲሉ አሳስበዋል።
በአዲስ አበባ የ2018 የክረምት ጎርፍ መከላከል እና የአደጋ ዝግጁነት ንቅናቄ ተጀመረ
Jun 23, 2026 127
አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የ2018 ክረምት ጎርፍ መከላከል እና የአደጋ ዝግጁነት ንቅናቄ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ፤ ንቅናቄው ክረምቱን ተከትሎ በሰው እና ንብረት ላይ ሊከሰት የሚችለውን ጉዳት አስቀድሞ መከላከልን ዓላማ ያደረገ ነው ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ ከዚህ ቀደም የአደጋ ተጋላጭነትን በአግባቡ አጥንቶ ዘላቂ መፍትሔ ሲሰጥ መቆየቱን አመላክተዋል። በዚህም ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ወንዞች የንጹህ ውሃ መውረጃ እንጂ የሰው ህይዎት የአደጋ መንስዔ ሊሆኑ እንደማይገባ አመልክተው፤ በቀጣይ ወንዞች የአደጋ መንስኤ እንዳይሆኑ በወንዝ ዳርቻ ልማት በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል። በምከትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው፤ በመዲናዋ ከአደጋ ተጋላጭነት ነጻ ከባቢን ለመፍጠር ሰፋፊ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህም ከዚህ ቀደም የአደጋ መንስዔ የነበሩ አካባቢዎች ወደ ምቹና ተመራጭ የመኖሪያ ስፍራነት መቀየራቸውን አመላክተዋል። በቀጣይም ከተማዋን ምቹ እና ለኑሮ ተመራጭ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ጥበቃ ረገድ ጠንካራ ርዕይና አመርቂ አፈጻጸም አላት-ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)
Jun 23, 2026 159
አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ጥበቃ ረገድ ጠንካራ ርዕይና አመርቂ አፈጻጸም እንዳላት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኮፕ32 ተሰያሚ ፕሬዚዳንት የሆኑት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። ቻተም ሃውስ የተሰኘው ዓለም አቀፍ ተቋም በለንደን ያዘጋጀውና “በተከፋፈለ ጂኦ-ፖለቲካዊ ሁኔታ ውስጥ የኮፕ ጉባኤዎችን አስፈላጊነት ማጉላት” በሚል ርዕስ በተካሄደው የአየር ንብረት ሳምንት የውይይት መድረክ ላይ ተካሂዷል። በመድረኩም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኮፕ32 ተሰያሚ ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ፣የኮፕ30 ፕሬዚዳንት አንድሬ ኮሬያ ከብራዚል እንዲሁም የኮፕ31ን የወከሉት የቱርክ የአካባቢ፣ የከተማ ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር በውይይቱ ላይ ተሳትፈዋል። ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ጥበቃ ረገድ ያላትን ጠንካራ ርዕይ እና አመርቂ አፈጻጸም አንስተዋል። በተለይም ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በፖሊሲ ተደግፈው ተግባራዊ የተደረጉ አፈጻጸሞችን አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል። የኮፕ32 ተሰያሚ ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ አክለውም፥ ኢትዮጵያ በምታዘጋጀው የኮፕ32 ቀዳሚ ተግባራት፣በቱርክና አውስትራሊያ በጋራ ከሚዘጋጀው የኮፕ31 የተገኙ ውጤቶች በመነሳት፣ ቀጣይነትን ማረጋገጥ እንደሚሆን ጠቁመዋል። ይህ አካሄድም ከኢትዮጵያ በፊት የኮፕ ጉባኤዎችን ካዘጋጁት ጋር በቅንጅት በመስራት፣ የጋራ ተግባራትን ማጠናከር መሆኑን ጠቁመዋል። እንዱሁም በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ሂደት ላይ ያለውን ተስፋ መልሶ ማቀጣጠል የሚለውን የ“መደመር” መርህ እንደሚያንጸባርቅ አፅንዖት ሰጥተው ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 11062
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 8179
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 6997
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 6898
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes)
Jun 23, 2026 220
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው · ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ሕጻናት ላይ የትኛው የስኳር ህመም ነው በስፋት እየተከሰተ ያለው? በሕጻናት ላይ የሚከሰቱ የተለያዩ የስኳር ህመም ዓይነቶች መኖራቸውን የሚገልጹት የሕጻናት የስኳር ህመም ስፔሻሊስት ዶክተር ሰውአገኝ የሺዋስ፤ እንደሀገራችን ግን በዋናነት የሚጠቀሰው ዓይነት አንድ የሚባለው የስኳር ህመም ነው ይላሉ። በአደጉ ሀገራት ላይ ዓይነት ሁለት የስኳር ህመምም በሕጻናት ላይ እንደሚከሰት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም ባብዛኛው እንቅስቃሴ ካለማድረግ፣ ከኑሮ ዘይቤ እንዲሁም ከመጠን ባለፈ ውፍረትና ተያያዥ ጉዳዮች ምክንያት የሚከሰት መሆኑንም ያስረዳሉ። ይሁን እንጅ በእኛ ሀገር ደረጃ ይህ (ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም) በስፋት በሕጻናት ላይ እንደማይስተዋልና ብዙም አሳሳቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። በዋናነት በእኛ ሀገር ሕጻናት ላይ እየተከሰተ ያለው ዓይነት አንድ የስኳር ህመም መሆኑን ገልጸው፤ተገቢው ጥንቃቄ ባለመደረጉ ልጆች ለውስብስብ ችግር እየተዳረጉ ነው ብለዋል። እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የጡት ካንሰርን ለመከላከል ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? · ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም አጋላጭ ምክንያቱ ይታወቃል? እንደ ባለሙያው ገላጸ፤ ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም አጋላጭ መንስዔው አይታወቅም። ይህን ተከትሎም አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል ሕክምና የለም። እንደ አጋላጭ ከሚታሰቡት መከካል ግን፤ ልጆች በተፈጥሮ ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም የመጋለጥ ዕድላቸው ከፍተኛ መሆኑ እና ውጫው (አካባቢያዊ ሁኔታዎች) በምክንያትነት ይነሳሉ ብለዋል። በእነዚህ ምክንያቶች በእያንዳንዱ የሰውነት እንቅስቃሴ ውስጥ ስኳር እንዲዋሃድ የሚያደርገው ኢንሱሊን የተሰኘ ሆርሞን መመረቱ ይቆማል፤ የኢንሱሊን እጥረት ሲያጋጥም ደግሞ ስኳር ደም ላይ እየጨመረ ይሄዳል፤ ደም ከ180 በላይ ከፍ በጊዜም ኩላሊት ወደ ውጭ ያስወግደዋል፤ በዚሁ ወቅትም ጠቃሚ ንጥረ ቅመሞች ጭምር ከሰውነት ይወገዳሉ፤ የፈሳሽ እጥረትም ያጋጥማቸዋል፤ ከዚያም የልጆች የሰውነት ክብደት መቀነስና ቶሎ ቶሎ (ከመደበኛው የተለየ) የመሽናት ሁኔታ ይከሰታል ሲሉ አብራርተዋል። · ዓይነት አንድና ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም እንደ ዶክተር ሰዋገኝ ማብራሪያ፤ ዓይነት አንድ እና ዓይነት ሁለት የስኳር ህመሞች የተለያዩ ናቸው። ዓይነት አንድ የስኳር ህመም ማለት፤ ኢንሱሊን በሰውነት ውስጥ ሳይመነጭ ሲቀር የሚከሰት መሆኑን አስረድተዋል። ይህን ህመም ቀድሞ መከላከል አይቻልም፤ ሲከሰት ሕክምና ማግኘት እንጅ ይላሉ። ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም፤ ኢንሱሊን የማመንጨት ችግር ሳይሆን፤ ኢንሱሊኑ በሰውነት ውስጥ ሳይሠራ ሲቀር የሚከሰት ነው ይላሉ። ይህም ከሰውነት ክብደት መጨመር፣ አካላዊ እንቅስቃሴ ባለማድረግ ምክንያት የሚመጣ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲውም ብዙ ጊዜ በዐዋቂዎች ዘንድ በስፋት የሚስተዋል ህመም መሆኑንም አመላክተዋል። ይህን ህመም አመጋገብን በማስተካከል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ፣ የኑሮ ዘይቤን በማስተከከል ቀድሞ መከላከል እንደሚቻልም ነው ያስገነዘቡት። · የስኳር ህመም በየትኛው የዕድሜ ክልል ይከሰታል? ዓይነት አንድ የስኳር ህመም የ6 ወር ዕድሜ ካለው ሕጻን ጀምሮ እስከ በዐዋቂነት የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ዶክተር ሰውአገኝ ይናገራሉ። ይህን ሲያብራሩም በተለይም ከ30 ዓመት በታች ባሉት የዕድሜ ክልሎች (በተለይም ከ5 - 7 እንዲሁም ከ14 - 15 ዓመት) ባሉ ልጆች ላይ በስፋት ከሰታል ብለዋል። · ምልክቶቹ በውል ይታወቃሉ? በአብዛኛው ከተለመዱ ምልክቶች መካከል፤ ቶሎ ቶሎ ውኃ መጠጣት፣ የማይረካ የውኃ ጥማት መኖር፣ ከወትሮው የተለየ ሌሊትን ጨምሮ ሽንት የመሽናት፣ ክብደት መቀነስ የሚሉት እንደሚገኙበት ይገልጻሉ። እነዚህ ምልክቶች ሲታዩም ጊዜ ሳያባክኑ (ህመሙ ሥር ሳይሰድ) ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ ተገቢ መሆኑን መክረዋል። በዚህ ሂደት ልጆች ህመማቸውን ዐውቀውና ራሳቸውን ችለው ወደ ሕክምና ተቋም እንደማይሄዱ ስለሚታወቅ ወላጆች (አሳዲዎች) ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ሾተላይን ቀድሞ መከላከል ይቻላል? · ሕክምና እና ምክረ ሐሳብ ምንም እንኳ አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል የታወቀ ነገር ባይኖርም ዓይነት አንድ የስኳር ህመም፤ ቶሎ ከታወቀና ሕክምና ከተደረገለት ልጆች እንደማንኛውም ጤናማ ልጅ ዕድገታቸው ይቀጥላል፣ ትምህርታቸውን መማር፣ ኑሯቸውን መቀጠል ይችላሉ። ልጆች በጊዜው (ህመሙ እንደተከሰተ ወዲያውኑ) ካልታከሙ ሕይዎታቸውን እስከማጣት የሚደርስ ውስብስብ ችግር የሚፈጥር መሆኑን ገልጸው፤ ወላጆች (አሳዳጊዎች) የልጆቻቸውን ጤና በአግባቡ እንዲከታተሉ መክረዋል።የተለየ ምልክት ሲያስተውሉም ወደ ሕክምና መሄድን መክረዋል። ምንም እንኳን አመጋገብን ማስተካከል ለጤና እንደ ግብዓት ተጠቃሚ መሆኑ ቢታመንም፤ ዓይነት አንድ የስኳር ህመምን በአመጋገብ ብቻ እናስተካክላለን በሚል መዘናጋት ተገቢ እንዳልሆነ ሕብረተሰቡ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል። በአመጋገብ ብቻ እናስተካክላለን ማለት ቶሎ እንዳይታከሙ ጊዜ በማባከን የልጆችን ጤና በይበልጥ ማወሳሰብ በመሆኑ፤ አዋጩ መፍትሔ በሕክምና ኢንሱሊን መስጠት እና በተጨማሪ አመጋገብን ከኢንሱሊኑ ጋር ማጣጣም መሆኑን አስገንዝበዋል። #የጤና_ነገር #ኢዜአ #ኢንሱሊን #የስኳር_ህመም #ሕጻናት
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Jun 21, 2026 836
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 14/2018 (ኢዜአ) ፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? በሳምንቱ ቢሾፍቱ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከባሕር ጠለል በላይ በ1 ሺህ 910 ሜትር ከፍታ ላይ በምትገኘው ቢሾፍቱ ግንባታው በመከናወን ላይ ይገኛል። የኤርፖርቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ግዙፍ የልማት ፕሮጀክት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የቢሾፍቱ ኢርፖርት ኢትዮጵያን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ማዕከላት ተርታ ለማሰለፍ የሚያስችል ታሪካዊ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ሳምንት ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በስፍራው በመገኘት የግንባታውን ሂደት የተመለከቱ ሲሆን ግንባታውን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅም ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ጥረት እየተገነባ ይገኛል ብለዋል። በእለቱም የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በቢሾፍቱ ያስጀመሩ ሲሆን ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞች የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጎሮ ወረዳ በመገኘት የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያስጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክትም ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው! ስለሆነም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በዚህ ሥራ እንዲሳተፍ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል። የሀገር መከታና የህዝብ አለኝታ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የህዝብ ወገንተኝነቱንና እና አለኝታነቱን በተግባር ማሳየቱን ቀጥሎበታል። ሰራዊቱ በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ ህዝባዊ ሰራዊት መሆኑን አሳይቷል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ተላላቅ መርሃ ግብሮች ባከበረበት ወቅት በሰሜን ጎንደር ዞን የ"ጭና ሰማዕታት መታሰቢያ ጤና ጣቢያ" ገንብቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ አስረክቧል። በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰራዊቱ የጀግንነት ታሪክ እንደ ውቅያኖስ የማይነጥፍ ከመሆኑም በላይ፣ በጭና ግንባር የተቀዳጀው ድል የጠላትን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅም ሙሉ በሙሉ የሰበረ የድል ማህተም ነው ብለዋል። ለልማት- የሃይል አማራጭን ማስፋት በኢትዮጵያ ከከተማ እስከ ገጠር የተሰናሰለ የሃይል ልማትን በማስፋት አማራጭ የሃይል አቅርቦት ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዚህ ሳምንትም በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ ከ312 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችል የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ለመገንባት መሰረተ ድንጋይ ተቀምጧል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሡልጣን ወሊ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጥረት በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ለዘላቂ ልማትና ለዜጎች ተጠቃሚነት የሃይል አማራጭን የማስፋት ስራ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አንስተዋል። በምርታማነት የምግብ ስርዓት ችግርን መፍታት በኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ችግርን ለመፍታት እስከ ታችኛው መንግስታዊ መዋቅር ድረስ የሚዘልቁ የተለያዩ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በዚሁ መሰረትም በምግብ ስርዓት አለመስተካከል የሚከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገልጿል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት በክልሉ ስርዓት ምግብ ሽግግርና የቀዳማዊ ልጅነት ልማት ፍኖተ ካርታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ችግር ፈች ምርምር ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በምርምር ሥራዎችና በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጸውም በዚህ ሳምንት ነው። በዩኒቨርሲቲው በምርምር ፕሮጀክቶች እና በማህበረሰብ አገልግሎቶች የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምግምና ቅንጅታዊ ሥራን ለማጠናከር ያለመ መድረክም አካሄዶ ነበር። መድረኩ በተለይ ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ዕድሎችን አስፍቶ ለመጠቀም የተመራማሪዎችን አቅም ማሳደግ ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ ከ84 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ 54 የምርምር ሥራዎችን እንዲሁም 70 የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። በቀብሪ በያህ ከተማ የወጣቶች የልማት ተጠቃሚነት በሶማሌ ክልል የልማትና የምርታማነት አጀንዳዎች በውጤታማነት ቀጥለዋል። የወጣችንና አጠቃላይ የክልሉን ህዝብ የልማት ፍላጎት መሰረት አድርገው እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው። በዚሁ መሰረት በክልሉ ፋፈን ዞን ቀብሪ በያህ ከተማ በማህበር ተደራጅተው ሥራ የፈጠሩ ወጣቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። አብዲከሪን መሀመድ እና ጓደኞቹ በማህበር ተደራጅተው በዶሮ እርባታ በመሰማራት በሌማት ትሩፋት የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። ሥራውን ከጀመሩ ወዲህ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ ለሌሎች ወገኖችም ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙ ይናገራሉ። እንደ አጠቃላይ በሶማሌ ክልል ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ቀጥለዋል። የበጀት ክለሳ በዚሁ ሳምንት የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የ2018 የበጀት ዓመት የ11 ወራት እቅድ አፈጻጸም መነሻ በማድረግ የቀረበለት የበጀት ክለሳ አፅድቋል። ካቢኔው በክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አማካኝነት የቀረበለትን ከ301 ሚሊየን 693 ሺህ 178 ብር የበጀት ክለሳ ነው ተወያይቶ ያፀደቀው። የበጀት ክለሳው በተለይም የፊስካልና ፋይናንሻል አፈፃፀማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ፕሮጀክቶችን በመለየት የላቀ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ላላቸውና የበጀት እጥረት ላጋጠማቸው ጉዳዮች የሚውል ነው ተብሏል። የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮቿን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት ልትሰጠው እየተጋች ነው። ለዚህ ዋና ማሳያው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ነው። ማዕከሉ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን የተገነባውን ኮንታ መሶብ የአንድ ማዕከል መርቀው በይፋ አገልግሎት አስጀምረዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል በተበታተነ ሁኔታ ይሰጡ የነበሩ የመንግሥትና የማኅበራዊ አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር በማሰባሰብ ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው። የኮንታ ማዕከልም ሕዝቡ ከቢሮ ወደ ቢሮ በመዘዋወር የሚያጠፋውን ጊዜ፣ ወጪና እንግልት በእጅጉ በመቀነስ ጥራት ያለው፣ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት እንዲያገኙ ያግዛቸዋል ተብሏል። የስደተኞች መጠጊያ- ኢትዮጵያ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞች መጠጊያ የሆነችው ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የስደተኞች ቀን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ተከብሯል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ክልሉ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞችን ከመቀበል ባለፈ ስደተኞችን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በክልሉ አራት መጠለያ ጣቢያዎች ላይ ከ112 ሺህ በላይ ስደተኞች እንደሚገኙ ገልፀው፥ ስደተኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ጠንካራ መስተጋብር በመፍጠር በአብሮነት እየኖሩ ነው ብለዋል። ስደተኞች የውሃ፣ የትምህርት የጤናና ሌሎች የመሠረተ ልማቶችን ከተቀባዩ ማህበረሰብ እኩል ተጠቃሚ መሆናቸው የኢትዮጵያን ስደተኞች አያያዝ የተሻለ ተሞክሮ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ጋምቤላ የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አባላት በመጪው የህዝብ ውክልና ስራ ስምሪት ወቅት የሚያከናውኗቸውን ተግባራት በተመለከተ የኦሬንቴሽን ፕሮግራም አካሂዷል። የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ጁል ናንጋል፣ የህዝብ ውክልና ተግባር የምክር ቤት አባላት ዋና ሃላፊነት መሆኑን ገልፀው፣ አባላቱ ወደ ህዝቡ በመቅረብ የህብረተሰቡን ፍላጎት፣ ችግርና አስተያየት በአግባቡ በማሰባሰብ ለመንግስት አካላት ማድረስ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። ምክትል አፈ ጉባኤው እንዳሉት፣ የህዝብ ውክልና ስራ በዜጎችና በምክር ቤቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና የህዝብ ተሳትፎን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ያለው በመሆኑ አባላቱ በተሰጣቸው ኃላፊነት ትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። ድሬደዋ ድሬደዋ የመስኖ ግንባታ። 'በቆላማ አከባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም' በሁላሁሉል ገጠር ቀበሌ ውስጥ የከርሰ ምድር ውሃን በመጠቀም የተሰሩ የንፁህ መጠጥ ውሃና የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች፥ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) በተገኙበት ተመርቋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) እና የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ ግድቡን በመረቁበት ወቅት ከምንም በላይ ለሰው ልጆች ህይወት እጅግ አስፈላጊ የሆነውና፥ የአስተዳደራችን የገጠር ነዋሪ ህብረተሰብ መሠረታዊ ፍላጎትና የረጅም ዘመናት ምኞት የነበረውን፥ የውሃ ጥያቄ በጋራ ርብርብ መመለስ መቻል የሚሰጠው ደስታ እጅግ ልዩ ነው ብለዋል ከንቲባው። የድሬዳዋን ማህበረሰብ የምግብ ሉኣላዊነት የማረጋገጥ፣ አርሶአደሩ ነዋሪ ከራሱ አልፎ ለገበያ በማቅረብ ኑሮውን እንዲያሻሽል እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመስኖ ልማት ሥራዎችን እንዲያከናውን በማገዝ ረገድ ቀጣይነት ያለው ስራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። አፋር ሳምንቱ በአፋር ክልል በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ያሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ወጣቶች፣ ባህልና ስፖርት ቢሮ ያስታወቀበትም ነበር። የአፋር ክልል አብዛኛው ማህበረሰብ ከፊል አርብቶ አደርና አርብቶ አደር በመሆኑ፣ በየዓመቱ የሚከናወኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክፍተቶች ለመሙላት ትልቅ ሚና አላቸው። በተለይም የአየር ንብረት መለዋወጥ፣ የውሃ እጥረት እና አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎችን ተቋቁሞ ዘላቂ ልማት ለማምጣት የወጣቶችና የህብረተሰቡ የተቀናጀ አቅም ወሳኝ ግብዓት ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። ማጠቃለያ ሳምንቱ በሁሉም ክልሎች መደበኛ የልማት፣ የማህበራዊ እና የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው የቀጠሉበትም ነበር። በሁሉም ክልሎች የስድስተኛ እና ስምንተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተካሄዷል። በተመሳሳይ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ዝግጅት በሁሉም ክልሎች እየተከናወነ ይገኛል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jun 15, 2026 2689
በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉የተራሮች ስር ፈርጥ - ወልዲያ የዛሬው የወፍ በረር ምልከታችን የሚጀምረው የተራሮች ስር ፈርጥ በሆነችው ወልዲያ ከተማ በመገኘት ነው። ከደሴ በ120 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውና በረጃጅም ተራሮች የተከበበችው ወልዲያ ከተማ ከነበረችበት ጉስቁልና ወጥታ አሁን ላይ በውበት ፈክታ ትገኛለች። በሳምንቱ በዚህች ከተማ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኮሪደር ልማቷንና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፤ ተዘዋውረውም ጎብኝተዋል። በተለያዩ ታሪካዊና ባህላዊ ትውፊቶች ስሟ ጎልቶ የሚጠራው ወልዲያ እንደ ከዋክብት ፈክታ እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር እየተስፋፉ መሆኑን አንስተው በቀጣይ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ትገሰግሳለች ብለዋል። 👉የሸደር አዳሪ ትምህርት ቤት የሚቀጥለው መዳረሻችን በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን አውበሬ ወረዳ ሼደር ከተማ አዲስ የተገነባውን አዳሪ ትምህርት ቤት መመረቅ ይሆኗል። የትምህርት ቤቱን ግንባታ መርቀው ስራ ያስጀመሩት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ናቸው። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው፤ በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋት የተማረ ትውልድ ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በ138 ሚሊየን ብር የተገነባው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ስራ መጀመሩ ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል። 👉የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የበረራ ቅኝታችን ቀጥሎ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በመስኖ እየለማ ያለ የስንዴ ምርት የመጎብኘት እድል አግኝተናል። በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል መሰብሰብ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። የግብርና ሜካናይዜሽንን በስፋት በመጠቀም እንዲሁም ፈጠራን በማከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ጥረቱ በተሳካ መልኩ መቀጠሉን አንስተዋል። 👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ዓለም አቀፍ ክስተት ነው። ችግሩ በተለይም በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ ይገኛል። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መጠን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ መፍትሄ ለመስጠት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። በዚህ ረገድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት በሚከናወኑ ሥራዎች በምርምር እያገዙ ናቸው። በሂደቱ ውጤታማነት ላይ የሚመክር መድረክ በሰመራ በተደረገበት ወቅት የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ችግሩን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት በምርምርና በማማከር እያገዙ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሰዎች ህገወጥ ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ለህብረተሰቡ እየሰጡ ናቸው። 👉የኢትዮጵያ እያመረተች ነው በአማራ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እና ሌሎችም በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለውጭ ምንዛሬ አይነተኛ የገቢ ምንጭ መሆን አስችሏል ብለዋል። 👉መሶብ በአርባ ምንጭ፣ ዲላ እና ነቀምቴ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት በዚህ ሳምንት አርባ ምንጭ፣ እና ዲላ ከተሞች ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። የመሶብ ማእከላቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል። የዲጅታል አሰራርን በማስፋት ለዜጎች ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። 👉ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩ ስለመሆኑ ያነሳል። በመሆኑም ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን አደራጅቷል። በመሆኑም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በእለቱ ድምፅ መስጠት ካልቻሉት መካከል የሰሜን ምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በፊት ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፃቸውን ሰጥተዋል። በተመሳሳይ በአፋር ክልል እና በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያዎች የሚገኙ ዜጎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል። 👉የመኸር እርሻ ንቅናቄ በሲዳማ ክልል የመኸር እርሻን በንቅናቄ በመምራት የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡና ገበያን የሚያረጋጉ የግብርና ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በንቅናቄ መድረኩ ርእሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት መሬት ጦሙን እንዳያድርና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ እንዲሁም ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠት ምርታማነቱን ማሳካት አስችሏል። ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል የበልግ ሰብልን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። ይህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ በማምረት ገበያን ለማረጋጋትና ለኢንደስትሪዎች ግብአት ለማቅረብ ያስችላል ነው የተባለው። በምርት ዘመኑ የተያዘውን እቅድ ለማሳካትም አመራሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር ለውጤቱ መትጋት እንዳለበትም በውይይቱ ተነስቷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምርጥ ዘር ብዜትን በዓይነት፣ በመጠንና በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ ተችሏል። ቢሮው በግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ እና በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዘር ብዜት ዕቅድ አፈጻጸምና ዝግጅት ላይ ያተኮረ የባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ እንደገለጹት፤ በክልሉ የምርጥ ዘርን በጥራትና በመጠን ለአርሶ አደሩ በወቅቱ በማድረስ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል። ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ለኢንዱስትሪዎች በቂ ግብዓትን ለማቅረብና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር አግዟል። ተግባሩን በማስቀጠልም በ2017/18 የምርት ዘመን በክልሉ ከ2 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ30 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ማምረት መቻሉንም ገልጸዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት
Jun 14, 2026 2057
በኢዜአ ዐይን …! በሙሴ መለሰ አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው።በዚህ ሂደት ደግሞ የኢትዮጵያ ድንቅ ስራ የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊትአውራሪነት ይጠቀሳል። መርሐ-ግብሩ የጋራ ነው በሚል ዕሳቤ በርካቶችን በንቃት አሳትፎ ለዓለም የሚደርስ የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ዐሳይቷል። የደን ሽፋን መጠንን አሳድጓል። ይህም በዓየር ንብረት ለውጥ ላይ የራሱን ሚና እያበረከተ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአረንጓዴ ዐሻራ ሚና ልቆ ይነሳል። ይህም የተራቆተ መሬትን ወደ ነበረበት ከመመለስ፣ የውኃ ሀብት አሥተዳደርን ምቹ ከማድረግ እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ጋር የሚያያዝ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብሩ በዕድሜ፣ በጾታ፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሥራ ዘርፎች፣ በኑሮ ደረጃ፣ በሐይማኖት ሳትለይ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች እንዲሳተፉበት በማድረጓ በዘርፉ ስኬታማ ጉዞ ላይ ናት። ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀት ከመሆን አልፎ ለጎረቤቶቿ ችግኝ በመለገስ መርሐ-ግብሩ እንዲስፋፋ እየተጋችም ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ሲናገሩ፤ አረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያ ትላልቅ ነገር አስባ፣ ትላልቅ ነገር ተልማ፣ ትላልቅ ነገር አቅዳ እና ሕዝቦቿን አስተባብራ ማሳካት እንደምትችል ለሌሎቹ ማሳያ ነው ማለታቸውም ከላይ ያነሳነውን ሐሳብ ያዳብረዋል። በተጨማሪም አረንጓዴ ዐሻራ በልዩ ትኩረት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሳይቆራረጥ እየተሠራ መሆኑን፤ በየዓመቱም በሚተከሉ ችግኞች ብዛት፣ በሚተከልበት መሬት ስፋት እና በሚሳተፉ ታታሪዎች ቁጥር እያደገ መሆኑን ያመላክታል። በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች እየወጡ በችግኝ ተከላ መሳተፋቸው የሀገርን የጋራ ራዕይ ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ትንታኔዎች
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 3064
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ። ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…!
Jun 15, 2026 1779
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 7104
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው?
Jun 12, 2026 2762
የጤና ነገር … በዮሐንስ ደርበው የሰው ልጅ ሊሻሻሉ በሚችሉ እና በማይችሉ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ለልብ ህመም ሊጋለጥ እንደሚችል የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የአዋቂ የልብ ሕክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ብርሃኑ ሞገስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የልብ ህመም ከተወሳሰብ ዘላቂ የጤና እክል እስከ ድንገተኛ ኅልፈት ያደርሳል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ሰዎች ማሻሻል በሚችሏቸው (ሞዲፋይብል) እና ማሻሻል በማይችሏቸው (ነን ሞዲፋይብል ወይም ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች) ለልብ ህመም ሊጋለጡ እንደሚችሉ ዶክተር ብርሃኑ ይገልጻሉ። መሻሻል ከሚችሉ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል፤ ከፍተኛ ጭንቀት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ ከፍተኛ የደም ግፊት ህመም (በአግባቡ መድኃኒቱ ካልተወሰደ)፣ተገቢ ያልሆነ የስብ ክምችት፣ ከፍተኛ ውፍረት (ክብደት)፣ በቂ እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ጤናማ አመጋገብ አለመኖር እንዲሁም አብዝቶ ስኳር፣ ጣፋጭና አልኮል መጠቀም የሚሉትን ይጠቅሳሉ፡፡ እንዲሁም ሰዎች ማሻሻል ከማይችሏቸው (ተፈጥሯዊ) አጋላጮች መካከል፤ በቤተሰብ የሚተላለፍ መኖሩን፣ በዕድሜ መጨመር የሚከሰት መሆኑን (ለምሳሌ፡- ወንድ ከ45 ሴት ከ55 ዓመት በላይ ሲሆናቸው ለልብ ህመም ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩን) እንዲሁም ወንዶ ከሴቶች በይበልጥ ለልብ ህመም ተጋላጭ የመሆናቸው አጋጣሚ ሰፊ ሊሆን እንደሚችልም አብራርተዋል፡፡ በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የልብ ህመም ምልክቶች የደረት ውጋት በግራ በኩል ወይም መሐል ላይ፣ ከወትሮው የተለየ ድካም፣ ትንፋሽ ማጠር፣ ከመደበኛው የተለየ የልብ ምት መኖር፣ የሰውነት በተለይም እግር አካባቢ እብጠት፣ ራስን መሳት እና ሳል የልብና ተያያዥ ህመም ምልክት ሊሆኑ እንደሚችሉ አብራርተዋል። የልብን ጤናን ለመጠበቅ በተቻለ መጠን ጤናማ አመጋገብን መከተል እንደሚገባ የሚመክሩት ዶክተር ብርሃኑ፤ አትክልት ማዘውተር፣ ምግብ ሲዘጋጅም ፈሳሽ ዘይት መጠቀም፣ ስኳር፣ ጨው እና ጣፋጭ ነገሮችን መገደብ ከተቻለም ማስወገድ እንደሚገባ ይመክራሉ፡፡ አካላዊ እንቅስቃሴ ማዘውተር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ይህም ብስክሌት መንዳት፣ በእግር እንቅስቃሴ ማድረግ፣ ዋና መዋኘት፣ እስከሚያልብ እና የልብ ምት እስከሚጨምር ብሎም እስከሚደክሙ የአካል ብቃት መሥራት የልብን ጤና ለመጠበቅ አስተዋጽዖ አለው ነው ያሉት፡፡ ጤናማ የሰውነት ክብደት እንዲኖር ማድረግ ተገቢ መሆኑን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ “ቦዲ ማስ ኢንዴክስ (ቢ ኤም አይ)” ከ18 ነጥብ 5 እስከ 25 እንዲሆን ይመከራል ብለዋል፡፡ ሲጋራ አለማጨስ፣ አልኮል አለመጠቀም፣ የስኳር ህመምና ከፍተኛ ደም ግፊት ካለም የመድኃኒት አወሳሰድን አለማስተጓጎል፣ አመጋገብ ላይ ስብ አለማብዛትና አብዝቶ አለመቀመጥ የልብ ህመምን ለመከላከል እንደሚያግዙ ነው ያስረዱት፡፡ ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በታች የሆኑ ጤናማ ሰዎች ከአንድ እስከ ሦስት ዓመት ባሉ ጊዜያት አንድ ጊዜ፣ ዕድሜያቸው ከ45 በላይ የሆኑ በየዓመቱ እንዲሁም የልብ ህመም ያለባቸው እንደሁኔታው በየጊዜው ክትትል እንዲያደርጉም መክረዋል፡፡ ሰዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እራሳቸውን ከልብ ህመም እንዲጠብቁ መክረው፤ ከዚህ ያለፈ ችግር ሲኖር ቶሎ የሕክምና ክትትል ማድረግ እና “ዛሬ ነገ” በማለት ጊዜ እያባከኑ ህመሙ ውስብስብ ደረጃ እስኪደርስ መጠበቅ እንደማይገባቸው አሳስበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ጤና #የልብ_ህመም
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 2275
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 16416
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 9494
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 15255
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት
Jun 23, 2026 154
በዮሐንስ ደርበው ከሰብል ልማት አኳያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን ያደረገው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አሁን ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ነው። ከበርካታ ትሩፋቶቹ መካከልም የምርታማነት ማደግ ተጠቃሽ ነው።ይህን ተከትሎም የሕብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አድጓል። ይህን ሐሳብ በአኃዝ አስደግፎ ለማየት ያህል፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፊት (በ2010 ዓ.ም) በሔክታር የሚመረተው ስንዴ 22 ኩንታል፣በቆሎ 30 ኩንታል፣ ጤፍ 17 ኩንታል እንዲሁም ገብስ 23 ኩንታል ነበር። ከኢንሼቲቩ ትግበራ በኋላ ደግሞ (በ2017 ዓ.ም) ስንዴ በሔክታር 36 ኩንታል፣ በቆሎ 46 ኩንታል፣ ጤፍ 20 ኩንታል፣ ገብስ 30 ኩንታል ማምረት ተችሏል። በዚህም መሠረት በ2017 ዓ.ም 7 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር መሬት በስንዴ ሰብል በመሸፈን 280 ሚሊየን ኩንታል ማምረት ተችሏል። ስንዴን በትጋት በማምረትም ከውጭ ለማስገባት ይወጣ የነበረን 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል። በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ ከፍራፍሬ አኳያ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፍራፍሬው ዘርፍ ዕድገትም ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል። በዚህም ገበያውን ከማረጋጋት ባለፈ ሕብረተሰቡ (አምራቹ) ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ በዚያው ልክ እንዲያድግ አስችሏል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ አቮካዶን በቀዳሚነት ወደ ውጭ የምትልክ ሁለተኛዋ ሀገር እንድትሆን አስችሏታል። ከቡና ልማት መስፋፋት አኳያ ሌላኛው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በረከት የቡና ልማት መስፋፋትና የውጭ ምንዛሬ ማደግ ነው። ይህን በአሥረጂ አስደግፈን ብንመለከት፤ በ2011 ዓ.ም በ600 ሺህ ሔክታር ላይ ቡና ተተክሏል። 500 ሺህ ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል።738 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኝቷል። እንዲሁም በ2017 ዓ.ም 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ቡና ተተክሏል። 1 ነጥብ 58 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 2 ነጥብ 65 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ማግኘት ተችሏል። ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጋር በተያያዘ ለ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። ከላይ የተጠቀሱ ማሳያዎችን (ናሙናዎችን) ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በቀጥታ ለሕዝቡ ጥቅም የቆመ መርሐ-ግብር መሆኑን መገንዘብ አያዳግትም። ስለዚህ በቀጣይ ሕብረተሰቡ በዚህ ኢኒሼቲቭ ላይ ያለጠባቂነት በንቃት በመሳተፍ እና ባሕሉ በማድረግ ተጠቃሚነቱንም በዚያው ልክ ለማሳደግ መትጋት ይጠበቅበታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በቢሾፍቱ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ባለፉት ዓመታት 48 ቢሊየን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፤ በዘንድሮው መርሐ-ግብር ደግሞ 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምጧል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #ተስፋን_እንትከል
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም
Jun 5, 2026 12875
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰርን ለመከላከል ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች በወቅቱ ካልታከመ ለኩላሊት መድከም፣ ለደም መመረዝና ለሞት የሚያደርሰው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል