ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን የሚያስችል አቅም ገንብቷል
Aug 11, 2026 72
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አደረጃጀትና አቅም መገንባቱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ። የቋሚ ኮሚቴው አባላት የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ጎብኝተዋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ባለፉት አምስት ዓመታት ኮሚሽኑ የተሰጠውን ኃላፊነት እንዲወጣ ላደረገው ድጋፍና ክትትል የምስጋና መርሃ-ግብር ተካሂዷል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኮሚሽኑ ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ ለውጦችን አስመዝግቧል። የኮሚሽኑን ሪፖርት ከመገምገም ባለፈም ቋሚ ኮሚቴው የመስክ ምልከታ በማድረግ ያልተቋረጠ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። የአደጋ ስጋት አመራር ፖሊሲን ከመከለስ ባለፈ የአዋጅ ማሻሻያ መደረጉን አንስተው፤ የተለያዩ ደንቦችም ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ ዜጎች ከተረጂነት አስተሳሰብ ተላቀው ወደ አምራችነት እንዲሸጋገሩ የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ ኮሚሽኑን በአዳዲስ አሰራሮችና በአዋጅ እንዲደራጅ በማድረግ በኢትዮጵያ ሊደርስ የሚችልን አደጋ አስቀድሞ መከላከልና ሲደርስ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እንዲገነባ ተደርጓል ብለዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ራዕዩን ማሳካት የሚያስችሉ ተስፋ ሰጭ ጥረቶችን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኮሚሽኑ ራስን በምግብ በመቻል የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት አከናውኗል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኮሚሽኑ ባለፉት አምስት ዓመታት ተጨባጭ ለውጦችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ ከለውጡ በኋላ በአዳዲስ አሰራሮችና ህጎችን በማሻሻል ሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን በራስ አቅም ማረጋገጥ የሚያስችል ውጤት አምጥቷል ብለዋል፡፡
ሀገርን ለመገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች እየመነጩበት የሚገኘው የምክክር ጉባኤ
Aug 11, 2026 109
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተሻለች ሀገርን ለመገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች እየመነጩበት መሆኑን ወጣት ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣት ተመካካሪዎች እንዳሉት፤ አሁን እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሂደት በሀገሪቱ የቆዩና ዘላቂ መፍትሔ ያላገኙ መሠረታዊ ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው። ከመድረኩ የሚወጡ የጋራ ሀሳቦች ለተሻለች ሀገር ግንባታና ለትውልድ መሻገሪያ የሚሆኑ መፍትሔዎችን እንደሚያስገኙም እምነታቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም ሂደቱ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም፣ ወንድማማችነትና አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት አስታውቀዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ወንድማገኝ ገርሶ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ይህ ምክክር ሁሉንም አካላት አሳታፊ ያደረገ መሆኑን ጠቁሟል። ምክክሩ በሀገሪቱ የነበሩ ግጭቶችን ለማስቀረትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እጅግ ተገቢና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጿል። ሂደቱ የሃሳብ የበላይነት የሚከበርበት፣ አንዱ ሌላውን በማከበር ሃሳቡን በነጻነት የሚያቀርብበት መልካም ሁኔታ መፈጠሩን አስታውቋል። በሂደቱ አማካኝነት ሰላሟ የተረጋገጠ፣ ያደገች፣ የለማችና ሕዝቦቿ በጋራ በፍቅርና በወንድማማችነት የሚኖሩባትን ኢትዮጵያን ማየት እንደሚመኝና እንደሚጠብቅ ተናግሯል። ሌላኛው ተመካካሪ ወጣት ቢኒያም ትግስቱ በበኩሉ፤ እየተካሄደ ያለው የምክክር ሂደት ሁሉንም አካላት ያካተተና አሳታፊ መሆኑን አንስቷል። ይህም የነገዋን ኢትዮጵያ በጸና መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችሉ በጎ ሃሳቦች የተቀኙበት መድረክ እንዲሆን ማድረጉን ጠቅሷል። ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተና እያደገ መምጣቱን አንስቶ፤ የተሻገረችና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ ጠቃሚ ሃሳቦች እየመነጩበት እንደሚገኝ ገልጿል። መድረኩ ማንኛውም ሃሳብ በነጻነት እየተንጸባረቀበት መሆኑን ያነሳው ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ ወጣት አይፈርስም በላይነህ ነው። የምክክር መድረኩ የነገዋን ጠንካራ ኢትዮጵያ ለመገንባት ትልቅ መፍትሔ ያመጣል ሲል ተናግሯል። በተጨማሪም ተመካካሪዎች በጋራ የሚደርሱባቸውን ስምምነቶች ሕዝቡም ተቀብሎ ተግባራዊ እንደሚያደርጋቸው ትልቅ ተስፋ እንዳለው ገልጿል።
በድሬዳዋ አስተዳደር የወባና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን የመከላከል ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል
Aug 11, 2026 96
ድሬደዋ፣ ነሃሴ 5/2018(ኢዜአ) ፡-በድሬዳዋ አስተዳደር የወባና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን የመከላከል ተግባር በተቀናጀ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉን የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ገለጸ። የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፅጌረዳ ክፍሌ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፤ አስተዳደሩ የወባና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን የመከላከል ተግባር በተቀናጀ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚህም የወባ እና የደንጊ ትኩሳት በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። በተለይ የወባ ትንኝ መራቢያ በሆኑ ቦታዎች ላይ የፀረ-ትንኝ ኬሚካል ርጭት በማካሄድና ውኃ ያቆሩ ስፍራዎችን በማጽዳት ረገድ ሰፊ የሕብረተሰብ ንቅናቄ ሥራ በመሥራት የአጎበር ስርጭት መካሄዱን ጠቁመዋል። በወባ በሽታ የሚያዙ ወገኖችም ፈጣን ሕክምና እንዲያገኙ ከመደረጉም በላይ፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ስለ በሽታው መከላከል የግንዛቤ ማስጨበጥና የቅኝት ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በአስተዳደር ደረጃ የወጣውን የጽዳት ሕግ በተቀናጀ መንገድ በመተግበር የወባና ተላላፊ በሽታዎችን ከመከላከል ባሻገር፣ ጽዱ ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ብለዋል። በተጨማሪም በገጠርና በከተማ በሚገኙ የጤና ተቋማት ወባን ከመከላከል ባሻገር፣ በተላላፊ በሽታዎች የተያዙ ሰዎችን አክሞ የማዳን ኃላፊነት በላቀ ዝግጁነትና ብቃት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
የዘላቂ የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን- የሃይማኖት አባቶች
Aug 11, 2026 91
ገንዳ ውኃ፤ ነሐሴ 5/ 2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን የዘላቂ የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድርሻቸውን እንደሚወጡ የሃይማኖት አባቶች ገለጹ። ይህ የተገለጸው "የሃይማኖት አባቶች ሚና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ" በሚል መሪ ሃሳብ በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ ነው። የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑት መልዓከ ኤዶም ማህቶት ማንደፍሮ፣ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በሚከናወኑ ተግባራት የሃይማኖት አባቶች የላቀ ሚናችንን በተደራጀ መልኩ መወጣት ይጠበቅብናል ብለዋል። በዚህም አብሮነትና ወንድማማችነት እንዲጠናከር የማድረግ ስራን አጠናክረን እንቀጥላለን በማለት አክለዋል። ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን በመገንዘብ፣ ማህበረሰቡ ከተሳሳቱ መረጃዎችና አሉባልታዎች ተጠብቆ፣ በእውነት ላይ የተመሠረተ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ በትብብር እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሌላኛው ተሳታፊ ሼክ ሙሐመድ አብዱልከሪም በበኩላቸው፣ "ህዝቡ እርስ በእርስ በመከባበርና በመደጋገፍ ለአካባቢው ሰላም መከበር የድርሻውን እንዲወጣ የማስተማርና የማንቃት ኃላፊነታችንን እንወጣለን" ብለዋል። መምህር ዳኘ አዲስ በበኩላቸው፣ "ለእውነተኛ ሰላም መስፈን በመቻቻል፣ በቅንነትና በወዳጅነት ተባብሮ መኖር ይገባል" በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ህዝቡ የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ ግዴታው እንደሆነ በመገንዘብ፣ የሃይማኖት ትምህርቶች በጥልቀትና በስፋት መስጠታችንን አጠናክረን መቀጠል ይገባናል ሲሉም አስገንዝበዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ ከንቲባ ተወካይ አቶ አዳነ ሀሰን፣ "የሃይማኖት አባቶች ሰላምን ለማስፈንና ማህበራዊ አብሮነትን ለማጠናከር እስካሁን ያደረጉትን በጎና ሚዛናዊ አስተዋጽኦ አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል" ብለዋል። ዘላቂ ሰላምን እውን ማድረግ የሚቻለው ማህበረሰቡን በእውነትና በደግነት መንገድ ላይ በመምራት መሆኑን ጠቅሰዋል። ሰላምን፣ መቻቻልን እና አብሮነትን በመስበክ ረገድ የእምነት አባቶች እያበረከቱት ያለውን ሚና አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ነው ያሉት። ህዝቡን ከከፋፋይ ንግግሮች፣ ከተሳሳቱ መረጃዎችና አሉባልታዎች በመጠበቅ፣ እውነትንና ፍቅርን መሰረት ያደረገ ግንዛቤ በማህበረሰቡ ዘንድ መፍጠር እንደሚጠበቅባቸውም አብራርተዋል።
በምስራቅ ሸዋ ዞን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የግብርና ምርቶች ኤክስፖርትን ለማሳደግ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል
Aug 11, 2026 267
አዳማ፤ ነሐሴ 5/2018(ኢዜአ) ፡-በምስራቅ ሸዋ ዞን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የግብርና ምርቶች ኤክስፖርትን ለማሳደግ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ ገለፁ። የምስራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የዞኑ አመራሮች በቦሰት ወረዳ በኩታገጠም የለማውን የቦሎቄና በቆሎ ሰብል ያለበትንና የእንክብካቤ ሂደትን ጎብኝተዋል። አቶ አባቡ ዋቆ በወቅቱ እንዳሉት፤ በዞኑ በምግብ ራስን ለመቻልና የኤክስፖርት ምርቶችን ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት እየሰራን ነው። በዞኑ በ2018/19 የምርት ዘመን ከ580 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዋና ዋና ሰብሎች በቴክኖሎጂ በታገዘ አሰራር በዘር መሸፈኑን ለአብነት አንስተዋል። በተለይም በዘንድሮው ዓመት የአርሶአደሩን ምርትና ምርታማነት ለመጨመር የሜካናይዜሽን አገልግሎቱን በስፋት ለአርሶአደሩ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። አጠቃላይ በሰብል ከተሸፈነው የዞኑ መሬት ውስጥ ከ91 በመቶ በላይ በሜካናይዜሽን በመደገፍና ቴክኖሎጂን በመጠቀም በኩታገጠም የለማ መሆኑንም አንስተዋል። በዋናነት ከውጭ የሚገቡ የግብርና ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የኤክስፖርት ምርቶችን ለማሳደግ የተቀመጠውን ሀገራዊ ግብ እውን ለማድረግ በሚደረገው ሂደት ውስጥ የዞኑ ድርሻ የላቀ ነው ብለዋል። ለዚህም አርሶአደሩ ገበያ ተኮር ምርቶችን በተለይም ቦሎቄ፣ ማሾ፣ ሽንብራ እንዲሁም ስንዴን በስፋት በኩታገጠም እያለማ ይገኛል ብለዋል። በየደረጃው የሚገኙ የዞኑ አመራሮች በየዕለቱ በአርሶአደሩ ማሳ በመገኘት ቡቃያው የለበትን ሁኔታ በመመልከት በእንክብካቤው በተለይም በአረምና የሰብል በሽታን በመከላከል ላይ የተሟላ እገዛ ማድረግ የጉብኝቱ ዓላማ መሆኑንም ተናግረዋል። የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ መስፍን ተሾመ በበኩላቸው በዞኑ ከመደበኛው የሰብል ልማት በተጓዳኝ የግብርና ኤክስፖርት ምርቶች ላይ እየሰራን ነው ብለዋል። በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ88ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቦሎቄ በኩታገጠም መልማቱን ለአብነት አንስተዋል። ከዚህም ከሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ያሉት አቶ መስፍን፤ ከሚገኘው ምርትም 900 ሺህ ኩንታል ያህሉ ወደ ውጭ ይላካል ብለዋል። የኤክስፖርት ቦሎቄ ልማቱን አርሶአደሮቹ ከባለሀብቶች ጋር በኮንትራት እርሻ ውል እያለሙ መሆኑንም ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ሀገርን ለመገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች እየመነጩበት የሚገኘው የምክክር ጉባኤ
Aug 11, 2026 109
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተሻለች ሀገርን ለመገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች እየመነጩበት መሆኑን ወጣት ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣት ተመካካሪዎች እንዳሉት፤ አሁን እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሂደት በሀገሪቱ የቆዩና ዘላቂ መፍትሔ ያላገኙ መሠረታዊ ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው። ከመድረኩ የሚወጡ የጋራ ሀሳቦች ለተሻለች ሀገር ግንባታና ለትውልድ መሻገሪያ የሚሆኑ መፍትሔዎችን እንደሚያስገኙም እምነታቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም ሂደቱ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም፣ ወንድማማችነትና አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት አስታውቀዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ወንድማገኝ ገርሶ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ይህ ምክክር ሁሉንም አካላት አሳታፊ ያደረገ መሆኑን ጠቁሟል። ምክክሩ በሀገሪቱ የነበሩ ግጭቶችን ለማስቀረትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እጅግ ተገቢና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጿል። ሂደቱ የሃሳብ የበላይነት የሚከበርበት፣ አንዱ ሌላውን በማከበር ሃሳቡን በነጻነት የሚያቀርብበት መልካም ሁኔታ መፈጠሩን አስታውቋል። በሂደቱ አማካኝነት ሰላሟ የተረጋገጠ፣ ያደገች፣ የለማችና ሕዝቦቿ በጋራ በፍቅርና በወንድማማችነት የሚኖሩባትን ኢትዮጵያን ማየት እንደሚመኝና እንደሚጠብቅ ተናግሯል። ሌላኛው ተመካካሪ ወጣት ቢኒያም ትግስቱ በበኩሉ፤ እየተካሄደ ያለው የምክክር ሂደት ሁሉንም አካላት ያካተተና አሳታፊ መሆኑን አንስቷል። ይህም የነገዋን ኢትዮጵያ በጸና መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችሉ በጎ ሃሳቦች የተቀኙበት መድረክ እንዲሆን ማድረጉን ጠቅሷል። ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተና እያደገ መምጣቱን አንስቶ፤ የተሻገረችና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ ጠቃሚ ሃሳቦች እየመነጩበት እንደሚገኝ ገልጿል። መድረኩ ማንኛውም ሃሳብ በነጻነት እየተንጸባረቀበት መሆኑን ያነሳው ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ ወጣት አይፈርስም በላይነህ ነው። የምክክር መድረኩ የነገዋን ጠንካራ ኢትዮጵያ ለመገንባት ትልቅ መፍትሔ ያመጣል ሲል ተናግሯል። በተጨማሪም ተመካካሪዎች በጋራ የሚደርሱባቸውን ስምምነቶች ሕዝቡም ተቀብሎ ተግባራዊ እንደሚያደርጋቸው ትልቅ ተስፋ እንዳለው ገልጿል።
የጋራ መግባባትን ለማጠናከር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት የታሪክ ድልድይ - ሀገራዊ ምክክር
Aug 11, 2026 144
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ በመካሄድ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የጋራ መግባባትን ለማጠናከር እና የተሻለች ሀገርን ለመገንባት ትልቅ ተስፋ የተጣለበት የታሪክ ድልድይ ነው። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ 4 ሺህ የሕዝብ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በስፋት የተሳተፉበት ይህ መድረክ፤ የዜጎችን ሀሳብ በማቀናጀት የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ አብሮነት እና የጋራ መግባባትን ለማጠናከር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ወሳኝ ምዕራፍም ነው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች እንደሚሉት፤ ምክክሩ የጋራ መግባባትን በማጎልበት ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት ሰፊ ዕድል ከፍቷል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝደንት ጽህፈት ቤት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ሀገራዊ ምክክሩ ትልቅ የሆነ ታሪካዊ ማካፈያ ስርዓት ነው ብለዋል። ምክክሩ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል መግባባት ባልተደረሰባቸው ጉዳዮች ላይ በመምከር ወደ መፍትሄ ለመቅረብ የሚያስችል ትልቅ ስርአት ነው ብለዋል። ይህ ታላቅ ሁነት ባሳለፍነው የጦርነት ታሪክና አለመግባባትን በምክክር በመፍታት ሰላሟ የተረጋገጠና የልማት ጎዳና ላይ ባለችው ኢትዮጵያ መሃከል ያለ ልዩ የታሪክ ድልድይ ነው ብለዋል። ምክክሩ ከተለያየ አስተሳሰብ እና የአኗኗር ዘዬ የመጣውን ማህበረሰብ እርስ በእርስ የመተዋወቅ እድልን አስፍቷል ብለዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ሜሪ ደስታ በበኩላቸው፤ በምክክሩ ተመካካሪዎች ሀሳባቸውን በነፃነት ለመግለጽ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን ገልጸው፤ የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሩም በሚያግባቡን ጉዳዩች ላይ በማተኮር እየተመካከርን ነው ብለዋል። ምክክሩ ለትውልዱ አንድነቷ የተጠናከረና የበለጸገች ሀገር የምናሻግርበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ሲሉም ተናግረዋል። ምክክሩ ከአጀንዳ አሰባሰብ ጀምሮ አሁን እስካለበት ሂደት ድረስ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች አካታችና አሳታፊ ያደረገ እንደነበር የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አብርሀም ሀይሌ ናቸው።
ዓባይና ቀይባህር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የሚያረጋግጡ መሠረቶች ናቸው - ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)
Aug 11, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ ዓባይና ቀይባህር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የሚያረጋግጡ መሠረቶች ናቸው ሲሉ የውሀ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። ዓባይና ቀይ ባሕር በኢትዮጵያ ታሪክ፣ ጂኦፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ የማይነጣጠሉና የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። ሁለቱ ውሀዎች በቀጣናው የፖለቲካ ካርታ ላይ የኃይል ሚዛን የሚወሰንባቸው ስትራቴጂካዊ የውሀ አካላት ናቸው። ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን ለማረጋገጥ የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በተከተለ መልኩ የዲፕሎማሲ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች ። የውሀ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ዓባይና ቀይባህር የኢትዮጵያን እጣፈንታ ሲወስኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያውያን ሕልውና ከእነዚህ የውሀ አካላት ጋር ከፍተኛ ቁርኝነት እንዳለውም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓባይን እንዳታለማና እንዳትጠቀም የውጭ ሃይሎች በተለያዩ መንገዶች ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን አመልክተው፤ በተመሳሳይ በሴራ ከቀይ ባህር እንድትርቅ በማድረግ ኢትዮጵያውያን ብዙ ዋጋ ሲከፍሉ መቆየታቸውን ጠቁመዋል። በህዳሴ ግድብ አማካኝነት ኢትዮጵያውያን ለዘመናት ሲመኙት ከነበረው ህልማቸው መካከል አንዱን ማሳካት መቻሉን ገልጸው፤ ይህም በኢትዮጵያውያን ላይ ይደርስ የነበረውን ተጽዕኖ መስበር ያስቻለ ስኬት መሆኑን አንስተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሀገሪቷ ላይ ሲደረጉ የቆዩ ደባዎችን ማስቀረት የቻለ የኢትዮጵያውያን ኩራት መገለጫ ፕሮጀክት መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ የቀይ ባህርን በተለያየ ሴራ እና ተንኮል እንድታጣ ከተደረገ በኋላ ይህንን ጉዳይ ማንሳት የማይፈቀድ እና ሌላ ስም የሚያሰጥ እንደነበርም አስታውሰዋል። ኢትዮጵያ አሁን ላይ የባህር በር ባለቤትነቷን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማግኘት አለብኝ ብላ ያነሳችው ጥያቄ ከፍተኛ የአመራር ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ጠቁመዋል። የቀይ ባህር ጉዳይ የመንግስት ወይም የአንድ ፖለቲካ ድርጅት ጉዳይ ሳይሆን ትውልድ ተሻጋሪ ስራ መሆኑን ጠቁመው፤ ዓባይና ቀይባህር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የሚያረጋግጡ መሠረቶች መሆናቸውን አንስተዋል። እንዲሁም በቀይባህር አቅራቢያ የሚታዩ ዓለም አቀፍ የጂኦ-ፖለቲካዊ ውድድሮች እና የባህር ላይ የደህንነት ስጋቶችን ማቃለል የሚያስችላት መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያውያን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ ያሳዩትን አንድነት በቀይ ባህር ላይም መድገም እንዳለባቸው አመልክተዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ የሀገርን ሰላምና ብልጽግና ለማረጋገጥ የጎላ አስተዋጽዖ ይኖረዋል
Aug 11, 2026 120
አምቦ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ የሀገርን እድገት ለማፋጠን እና ዘላቂ ሰላምን እውን ያደርጋል ብለው እንደሚጠብቁ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአምቦ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች አስታወቁ። ኢትዮጵያ ለዘመናት የዘለቁ የፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልዩነቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራዊ ምክክር የማጠቃለያ ጉባዔ በማካሄድ ላይ ትገኛለች። በምክክሩ የብዙሃን ድምፅ የሚሰማበት የተዛቡ የፖለቲካና የህብረተሰብ ተረኮች የሚታረሙበት እንዲሁም የጋራ የወደፊት ራዕይ የሚቃኝበት ታላቅ ሀገራዊ መድረክ እንደሆነም ይታመናል። የአምቦ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች እንደገለጹት፤ ምክክሩ ቀደም ሲል በፖለቲካ፣ በማኅበራዊና በሌሎች ዘርፎች በዜጎች መካከል የነበሩ አለመግባባቶችንና የግጭት መንስኤዎችን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል ብለው ተስፋ ያደርጋሉ። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ በቀለ ባይሳ፤ ምክክሩ ኢትዮጵያዊያን ልዩነቶቻቸውን በንግግር በመፍታትና የጋራ ሐሳቦችን በማጠናከር የሀገራቸውን ልማት ማፋጠን የሚችሉበት ዐውድ ላይ መድረሳቸውን ያሳያል ብለዋል። ለዓመታት ቅሬታና ግጭት ሲፈጥሩ የቆዩ የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄዎች በውይይት ሲፈቱ ሁሉም ዜጎች በአሸናፊነት ለሀገር እድገት የሚቆሙበት ሁኔታ ይፈጠራል የሚል እምነት እንዳላቸውም ተናግረዋል። አቶ በቀለ አክለውም፤ ችግሮችን ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት መመካከር ለነበሩት ችግሮቻችን መፍትሄ የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ የመምከር ባህልን በህዝቡ ዘንድ ያሰርጻል፤ የተሻለች ሀገርንም ለትውልድ ያሻግራል ብለዋል። ሌላኛው የከተማዋ የሀገር ሽማግሌና የምክክር ሂደቱ ተሳታፊ የሆኑት አቶ ባይሳ ጆብር በበኩላቸው፤ ሂደቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንና የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል። አቶ ፉፋ ቀቀባ የተባሉት የሀገር ሽማግሌ ደግሞ፤ ኢትዮጵያውያን የብሔርና የሃይማኖት ልዩነት ሳይበግራቸው በፍቅርና በመከባበር ባህል ለዘመናት አብረው የኖሩ ሕዝቦች መሆናቸውን አስታውሰዋል። በመሆኑም አጥፊና ከፋፋይ ጉዳዮችን በማስቀረት የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመገንባት የሚያስችል የምክክር ሂደት መሆኑን ጠቁመዋል። አካታች የሆነው ይህ ሀገራዊ ምክክር የሕዝቦችን ጥያቄ በውይይት የሚመልስ በመሆኑ፣ ሁሉም ዜጋ አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚገባም ጥሪ በማቅረብ፤ እሳቸውም የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
በከተማው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል
Aug 11, 2026 146
ደብረ ብርሃን ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የከተማው አስተዳደር ገለጸ። የከተማ አስተዳደሩ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም የግምገማ መድረክን እያካሄደ ነው። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በመድረኩ እንደገለጹት፤ በከተማ አስተዳደሩ በ2018 በጀት ዓመት ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል። ከተከናወኑ ሥራዎች መካከልም በጤና፣ በትምህርት፣ በገቢ አሰባሰብና በቱሪዝም ዘርፎች አበረታች ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። ለዚህም በየደረጃው ያለው አመራር ከኅብረተሰቡ ጋር በመናበብ ባከናወናቸው ተግባራት፣ በፓርቲና በመንግሥት ሥራዎች የተቀመጡ ግቦች በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወኑ ማስቻሉን ገልጸዋል። እንዲሁም በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት የሥራ ዘርፎች ለመሰማራት ፈቃድ ለጠየቁ 228 አዳዲስ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ገልጸው፣ ለባለሀብቶቹም 70 ሄክታር መሬት መተላለፉን ጠቅሰዋል። በከተማው እየተገነቡ የሚገኙ የኮሪደር ልማትና የአንድ መሶብ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትም በቀጣይ የሕዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሚያቃልል መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። የኑሮ ውድነትን ለማሻሻልም የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለኅብረተሰቡ በማቅረብ ገበያው እንዲረጋጋ የማድረግ ሥራ መከናወኑን አመልክተዋል። በ2019 በጀት ዓመትም የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎችን አቀናጅቶ በማከናወን የኅብረተሰቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሠራም አስታውቀዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰሎሞን ጌታቸው፤ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የተለያዩ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። ኅብረተሰቡ በከተማ አስተዳደሩ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶች ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆንና የአካባቢውን ሰላም ከፀጥታ ኃይሉ ጎን ሆኖ በመጠበቁ በከተማው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ አስችሏል ብለዋል። በውይይት መድረኩም የከተማ አስተዳደሩ፣ የክፍለ ከተማና የቀበሌ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የምክክር ጉባኤው በሀሳብ ብዝሃነት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ተስፋ ሰጪ ነው- ተመካካሪዎች
Aug 11, 2026 148
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5 /2018(ኢዜአ)፦የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን እያሳተፈ የሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ፣ የሀሳብ ብዝሃነትን በማንጸባረቅ ለጋራ መግባባትና ለዘላቂ ሰላም መሠረት የሚጥል ተስፋ ሰጪ ሂደት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች እንደተናገሩት፤ ምክክሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ ማህበረሰቦች እኩል ሀሳባቸውን እንዲያቀርቡ ዕድል በመስጠት አካታችነቱን እያረጋገጠ ነው። ከተመካካሪዎቹ መካከል አባገዳ ለሜቻ ለማ እንደገለጹት፤ በምክክሩ ላይ የተለያዩ ሀሳቦች በነፃነት እየቀረቡና እየዳበሩ ይገኛሉ። በምክክሩ ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ይህም በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን ደረጃ በደረጃ መፍታት የሚያስችል የመፍትሔ ሀሳብ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የጋራ መግባባት የተፈጠረባትና አንድነቷ የጸናች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላው ተመካካሪ ባዬ በሬ በበኩላቸው፤ ምክክሩ ከአካታችነት አንጻር ሁሉንም የሚያሳትፍና የሀሳብ ብዝሃነት የሚንጸባረቅበት መሆኑን ገልጸዋል። በምክክሩ ላይ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ሀሳቦች እየቀረቡ መሆናቸውን ገልፀው ፤ ይህም የተሻለ ነገን መገንባት እንደሚቻል እየታየ መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል በሚወክል መልኩ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አለሙ አሻግሬ (ዶ/ር) ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮችን በምክክር የመፍታት አዲስ ባህል መሆኑን ገልጸው፤ ሂደቱ ዛሬ ላይ ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ የምትሆን የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት እንደሚያስችል ጠቁመዋል።
የምክክር ጉባኤው የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክር ነው-የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
Aug 11, 2026 181
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክርና ኢኮኖሚ ዕድገትን ለማፋጠን የሚያስችል የጋራ መግባባት ይገነባል የሚል ተስፋ አለን ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በጉባኤውም በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች፣በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያውያን መካከል የጋራ መግባባትን በመፍጠር ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ወሳኝ መንገድ እንደሆነ ከፍተኛ እምነት አላቸው። የምክክር ሂደቱ የሀገርን አንድነት ለማጠናከር፣ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማሳደግ የሚያስችል የጋራ መግባባት እንደሚፈጥር ትልቅ ተስፋ የጣሉበት መሆኑንም ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ሮቤል ብርሃኑ፣ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን የሚገነባ አዋጭና ስልጡን አካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። በሀገራዊ ችግሮች ዙሪያ በአንድ ጣሪያ ሥር ምክክር ሲደረግ፣በመሠረታዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን ለመገንባት የሚያስችል ወሳኝ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በፖለቲካው መስክ መግባባትን በመፍጠር የሀገርን የኢኮኖሚ አቅም የሚገነባ የተረጋጋ የልማት ሥራን ለማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤም የኢኮኖሚ ዕድገትና የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክር የጋራ መግባባት የሚገነባ አዎንታዊ ምክረ ሐሳቦች የሚፈልቁበት እንደሚሆን ተስፋ አለኝ ብለዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ኃይሌ ዓለማየሁ በበኩላቸው፣ የአንድ ሀገር ዜጎች በጋራ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የምክክር ሐሳብ በመወጠን መሰባሰባቸው በራሱ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። ከዚህ ታሪካዊ መድረክ በኋላም የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያሳልጥ የጋራ መግባባትን በመገንባት፣ኢትዮጵያ በአፍሪካ ደረጃ መሪ ሀገር ለመሆን የሚያስችላትን አቅም እንደምትፈጥር እምነታቸውን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው አካታችነት በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን በመገንባት የሕዝብ አንድነትን ይበልጥ ያጠናክራል የሚል ተስፋ አለኝ ያሉት ደግሞ ያደታ ጉደታ ናቸው። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ አልማዝ ታምራት በበኩላቸው፣ የምክክር ጉባኤው በዜጎች መካከል ጠንካራ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት መሠረት የሚጥል የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የመዲናዋ ነዋሪ አስቻለው በርጋ እንዲሁ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የሚያግዝ ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል። አቶ ገረመው ደበበ በበኩላቸው፣ የሀገራዊ ምክክሩ ውጤትም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘላቂ ሰላምና የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የጋራ መግባባት ይፈጥራል የሚል እምነት አለኝ ብለዋል።
ፖለቲካ
ሀገርን ለመገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች እየመነጩበት የሚገኘው የምክክር ጉባኤ
Aug 11, 2026 109
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተሻለች ሀገርን ለመገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች እየመነጩበት መሆኑን ወጣት ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣት ተመካካሪዎች እንዳሉት፤ አሁን እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሂደት በሀገሪቱ የቆዩና ዘላቂ መፍትሔ ያላገኙ መሠረታዊ ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው። ከመድረኩ የሚወጡ የጋራ ሀሳቦች ለተሻለች ሀገር ግንባታና ለትውልድ መሻገሪያ የሚሆኑ መፍትሔዎችን እንደሚያስገኙም እምነታቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም ሂደቱ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም፣ ወንድማማችነትና አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት አስታውቀዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ወንድማገኝ ገርሶ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ይህ ምክክር ሁሉንም አካላት አሳታፊ ያደረገ መሆኑን ጠቁሟል። ምክክሩ በሀገሪቱ የነበሩ ግጭቶችን ለማስቀረትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እጅግ ተገቢና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጿል። ሂደቱ የሃሳብ የበላይነት የሚከበርበት፣ አንዱ ሌላውን በማከበር ሃሳቡን በነጻነት የሚያቀርብበት መልካም ሁኔታ መፈጠሩን አስታውቋል። በሂደቱ አማካኝነት ሰላሟ የተረጋገጠ፣ ያደገች፣ የለማችና ሕዝቦቿ በጋራ በፍቅርና በወንድማማችነት የሚኖሩባትን ኢትዮጵያን ማየት እንደሚመኝና እንደሚጠብቅ ተናግሯል። ሌላኛው ተመካካሪ ወጣት ቢኒያም ትግስቱ በበኩሉ፤ እየተካሄደ ያለው የምክክር ሂደት ሁሉንም አካላት ያካተተና አሳታፊ መሆኑን አንስቷል። ይህም የነገዋን ኢትዮጵያ በጸና መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችሉ በጎ ሃሳቦች የተቀኙበት መድረክ እንዲሆን ማድረጉን ጠቅሷል። ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተና እያደገ መምጣቱን አንስቶ፤ የተሻገረችና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ ጠቃሚ ሃሳቦች እየመነጩበት እንደሚገኝ ገልጿል። መድረኩ ማንኛውም ሃሳብ በነጻነት እየተንጸባረቀበት መሆኑን ያነሳው ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ ወጣት አይፈርስም በላይነህ ነው። የምክክር መድረኩ የነገዋን ጠንካራ ኢትዮጵያ ለመገንባት ትልቅ መፍትሔ ያመጣል ሲል ተናግሯል። በተጨማሪም ተመካካሪዎች በጋራ የሚደርሱባቸውን ስምምነቶች ሕዝቡም ተቀብሎ ተግባራዊ እንደሚያደርጋቸው ትልቅ ተስፋ እንዳለው ገልጿል።
የጋራ መግባባትን ለማጠናከር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት የታሪክ ድልድይ - ሀገራዊ ምክክር
Aug 11, 2026 144
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ በመካሄድ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የጋራ መግባባትን ለማጠናከር እና የተሻለች ሀገርን ለመገንባት ትልቅ ተስፋ የተጣለበት የታሪክ ድልድይ ነው። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ 4 ሺህ የሕዝብ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በስፋት የተሳተፉበት ይህ መድረክ፤ የዜጎችን ሀሳብ በማቀናጀት የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ አብሮነት እና የጋራ መግባባትን ለማጠናከር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ወሳኝ ምዕራፍም ነው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች እንደሚሉት፤ ምክክሩ የጋራ መግባባትን በማጎልበት ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት ሰፊ ዕድል ከፍቷል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝደንት ጽህፈት ቤት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ሀገራዊ ምክክሩ ትልቅ የሆነ ታሪካዊ ማካፈያ ስርዓት ነው ብለዋል። ምክክሩ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል መግባባት ባልተደረሰባቸው ጉዳዮች ላይ በመምከር ወደ መፍትሄ ለመቅረብ የሚያስችል ትልቅ ስርአት ነው ብለዋል። ይህ ታላቅ ሁነት ባሳለፍነው የጦርነት ታሪክና አለመግባባትን በምክክር በመፍታት ሰላሟ የተረጋገጠና የልማት ጎዳና ላይ ባለችው ኢትዮጵያ መሃከል ያለ ልዩ የታሪክ ድልድይ ነው ብለዋል። ምክክሩ ከተለያየ አስተሳሰብ እና የአኗኗር ዘዬ የመጣውን ማህበረሰብ እርስ በእርስ የመተዋወቅ እድልን አስፍቷል ብለዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ሜሪ ደስታ በበኩላቸው፤ በምክክሩ ተመካካሪዎች ሀሳባቸውን በነፃነት ለመግለጽ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን ገልጸው፤ የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሩም በሚያግባቡን ጉዳዩች ላይ በማተኮር እየተመካከርን ነው ብለዋል። ምክክሩ ለትውልዱ አንድነቷ የተጠናከረና የበለጸገች ሀገር የምናሻግርበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ሲሉም ተናግረዋል። ምክክሩ ከአጀንዳ አሰባሰብ ጀምሮ አሁን እስካለበት ሂደት ድረስ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች አካታችና አሳታፊ ያደረገ እንደነበር የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አብርሀም ሀይሌ ናቸው።
ዓባይና ቀይባህር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የሚያረጋግጡ መሠረቶች ናቸው - ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)
Aug 11, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ ዓባይና ቀይባህር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የሚያረጋግጡ መሠረቶች ናቸው ሲሉ የውሀ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። ዓባይና ቀይ ባሕር በኢትዮጵያ ታሪክ፣ ጂኦፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ የማይነጣጠሉና የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። ሁለቱ ውሀዎች በቀጣናው የፖለቲካ ካርታ ላይ የኃይል ሚዛን የሚወሰንባቸው ስትራቴጂካዊ የውሀ አካላት ናቸው። ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን ለማረጋገጥ የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በተከተለ መልኩ የዲፕሎማሲ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች ። የውሀ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ዓባይና ቀይባህር የኢትዮጵያን እጣፈንታ ሲወስኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያውያን ሕልውና ከእነዚህ የውሀ አካላት ጋር ከፍተኛ ቁርኝነት እንዳለውም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓባይን እንዳታለማና እንዳትጠቀም የውጭ ሃይሎች በተለያዩ መንገዶች ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን አመልክተው፤ በተመሳሳይ በሴራ ከቀይ ባህር እንድትርቅ በማድረግ ኢትዮጵያውያን ብዙ ዋጋ ሲከፍሉ መቆየታቸውን ጠቁመዋል። በህዳሴ ግድብ አማካኝነት ኢትዮጵያውያን ለዘመናት ሲመኙት ከነበረው ህልማቸው መካከል አንዱን ማሳካት መቻሉን ገልጸው፤ ይህም በኢትዮጵያውያን ላይ ይደርስ የነበረውን ተጽዕኖ መስበር ያስቻለ ስኬት መሆኑን አንስተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሀገሪቷ ላይ ሲደረጉ የቆዩ ደባዎችን ማስቀረት የቻለ የኢትዮጵያውያን ኩራት መገለጫ ፕሮጀክት መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ የቀይ ባህርን በተለያየ ሴራ እና ተንኮል እንድታጣ ከተደረገ በኋላ ይህንን ጉዳይ ማንሳት የማይፈቀድ እና ሌላ ስም የሚያሰጥ እንደነበርም አስታውሰዋል። ኢትዮጵያ አሁን ላይ የባህር በር ባለቤትነቷን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማግኘት አለብኝ ብላ ያነሳችው ጥያቄ ከፍተኛ የአመራር ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ጠቁመዋል። የቀይ ባህር ጉዳይ የመንግስት ወይም የአንድ ፖለቲካ ድርጅት ጉዳይ ሳይሆን ትውልድ ተሻጋሪ ስራ መሆኑን ጠቁመው፤ ዓባይና ቀይባህር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የሚያረጋግጡ መሠረቶች መሆናቸውን አንስተዋል። እንዲሁም በቀይባህር አቅራቢያ የሚታዩ ዓለም አቀፍ የጂኦ-ፖለቲካዊ ውድድሮች እና የባህር ላይ የደህንነት ስጋቶችን ማቃለል የሚያስችላት መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያውያን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ ያሳዩትን አንድነት በቀይ ባህር ላይም መድገም እንዳለባቸው አመልክተዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ የሀገርን ሰላምና ብልጽግና ለማረጋገጥ የጎላ አስተዋጽዖ ይኖረዋል
Aug 11, 2026 120
አምቦ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ የሀገርን እድገት ለማፋጠን እና ዘላቂ ሰላምን እውን ያደርጋል ብለው እንደሚጠብቁ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአምቦ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች አስታወቁ። ኢትዮጵያ ለዘመናት የዘለቁ የፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልዩነቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራዊ ምክክር የማጠቃለያ ጉባዔ በማካሄድ ላይ ትገኛለች። በምክክሩ የብዙሃን ድምፅ የሚሰማበት የተዛቡ የፖለቲካና የህብረተሰብ ተረኮች የሚታረሙበት እንዲሁም የጋራ የወደፊት ራዕይ የሚቃኝበት ታላቅ ሀገራዊ መድረክ እንደሆነም ይታመናል። የአምቦ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች እንደገለጹት፤ ምክክሩ ቀደም ሲል በፖለቲካ፣ በማኅበራዊና በሌሎች ዘርፎች በዜጎች መካከል የነበሩ አለመግባባቶችንና የግጭት መንስኤዎችን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል ብለው ተስፋ ያደርጋሉ። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ በቀለ ባይሳ፤ ምክክሩ ኢትዮጵያዊያን ልዩነቶቻቸውን በንግግር በመፍታትና የጋራ ሐሳቦችን በማጠናከር የሀገራቸውን ልማት ማፋጠን የሚችሉበት ዐውድ ላይ መድረሳቸውን ያሳያል ብለዋል። ለዓመታት ቅሬታና ግጭት ሲፈጥሩ የቆዩ የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄዎች በውይይት ሲፈቱ ሁሉም ዜጎች በአሸናፊነት ለሀገር እድገት የሚቆሙበት ሁኔታ ይፈጠራል የሚል እምነት እንዳላቸውም ተናግረዋል። አቶ በቀለ አክለውም፤ ችግሮችን ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት መመካከር ለነበሩት ችግሮቻችን መፍትሄ የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ የመምከር ባህልን በህዝቡ ዘንድ ያሰርጻል፤ የተሻለች ሀገርንም ለትውልድ ያሻግራል ብለዋል። ሌላኛው የከተማዋ የሀገር ሽማግሌና የምክክር ሂደቱ ተሳታፊ የሆኑት አቶ ባይሳ ጆብር በበኩላቸው፤ ሂደቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንና የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል። አቶ ፉፋ ቀቀባ የተባሉት የሀገር ሽማግሌ ደግሞ፤ ኢትዮጵያውያን የብሔርና የሃይማኖት ልዩነት ሳይበግራቸው በፍቅርና በመከባበር ባህል ለዘመናት አብረው የኖሩ ሕዝቦች መሆናቸውን አስታውሰዋል። በመሆኑም አጥፊና ከፋፋይ ጉዳዮችን በማስቀረት የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመገንባት የሚያስችል የምክክር ሂደት መሆኑን ጠቁመዋል። አካታች የሆነው ይህ ሀገራዊ ምክክር የሕዝቦችን ጥያቄ በውይይት የሚመልስ በመሆኑ፣ ሁሉም ዜጋ አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚገባም ጥሪ በማቅረብ፤ እሳቸውም የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
በከተማው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል
Aug 11, 2026 146
ደብረ ብርሃን ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የከተማው አስተዳደር ገለጸ። የከተማ አስተዳደሩ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም የግምገማ መድረክን እያካሄደ ነው። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በመድረኩ እንደገለጹት፤ በከተማ አስተዳደሩ በ2018 በጀት ዓመት ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል። ከተከናወኑ ሥራዎች መካከልም በጤና፣ በትምህርት፣ በገቢ አሰባሰብና በቱሪዝም ዘርፎች አበረታች ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። ለዚህም በየደረጃው ያለው አመራር ከኅብረተሰቡ ጋር በመናበብ ባከናወናቸው ተግባራት፣ በፓርቲና በመንግሥት ሥራዎች የተቀመጡ ግቦች በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወኑ ማስቻሉን ገልጸዋል። እንዲሁም በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት የሥራ ዘርፎች ለመሰማራት ፈቃድ ለጠየቁ 228 አዳዲስ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ገልጸው፣ ለባለሀብቶቹም 70 ሄክታር መሬት መተላለፉን ጠቅሰዋል። በከተማው እየተገነቡ የሚገኙ የኮሪደር ልማትና የአንድ መሶብ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትም በቀጣይ የሕዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሚያቃልል መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። የኑሮ ውድነትን ለማሻሻልም የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለኅብረተሰቡ በማቅረብ ገበያው እንዲረጋጋ የማድረግ ሥራ መከናወኑን አመልክተዋል። በ2019 በጀት ዓመትም የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎችን አቀናጅቶ በማከናወን የኅብረተሰቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሠራም አስታውቀዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰሎሞን ጌታቸው፤ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የተለያዩ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። ኅብረተሰቡ በከተማ አስተዳደሩ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶች ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆንና የአካባቢውን ሰላም ከፀጥታ ኃይሉ ጎን ሆኖ በመጠበቁ በከተማው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ አስችሏል ብለዋል። በውይይት መድረኩም የከተማ አስተዳደሩ፣ የክፍለ ከተማና የቀበሌ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የምክክር ጉባኤው በሀሳብ ብዝሃነት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ተስፋ ሰጪ ነው- ተመካካሪዎች
Aug 11, 2026 148
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5 /2018(ኢዜአ)፦የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን እያሳተፈ የሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ፣ የሀሳብ ብዝሃነትን በማንጸባረቅ ለጋራ መግባባትና ለዘላቂ ሰላም መሠረት የሚጥል ተስፋ ሰጪ ሂደት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች እንደተናገሩት፤ ምክክሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ ማህበረሰቦች እኩል ሀሳባቸውን እንዲያቀርቡ ዕድል በመስጠት አካታችነቱን እያረጋገጠ ነው። ከተመካካሪዎቹ መካከል አባገዳ ለሜቻ ለማ እንደገለጹት፤ በምክክሩ ላይ የተለያዩ ሀሳቦች በነፃነት እየቀረቡና እየዳበሩ ይገኛሉ። በምክክሩ ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ይህም በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን ደረጃ በደረጃ መፍታት የሚያስችል የመፍትሔ ሀሳብ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የጋራ መግባባት የተፈጠረባትና አንድነቷ የጸናች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላው ተመካካሪ ባዬ በሬ በበኩላቸው፤ ምክክሩ ከአካታችነት አንጻር ሁሉንም የሚያሳትፍና የሀሳብ ብዝሃነት የሚንጸባረቅበት መሆኑን ገልጸዋል። በምክክሩ ላይ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ሀሳቦች እየቀረቡ መሆናቸውን ገልፀው ፤ ይህም የተሻለ ነገን መገንባት እንደሚቻል እየታየ መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል በሚወክል መልኩ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አለሙ አሻግሬ (ዶ/ር) ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮችን በምክክር የመፍታት አዲስ ባህል መሆኑን ገልጸው፤ ሂደቱ ዛሬ ላይ ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ የምትሆን የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት እንደሚያስችል ጠቁመዋል።
የምክክር ጉባኤው የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክር ነው-የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
Aug 11, 2026 181
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክርና ኢኮኖሚ ዕድገትን ለማፋጠን የሚያስችል የጋራ መግባባት ይገነባል የሚል ተስፋ አለን ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በጉባኤውም በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች፣በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያውያን መካከል የጋራ መግባባትን በመፍጠር ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ወሳኝ መንገድ እንደሆነ ከፍተኛ እምነት አላቸው። የምክክር ሂደቱ የሀገርን አንድነት ለማጠናከር፣ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማሳደግ የሚያስችል የጋራ መግባባት እንደሚፈጥር ትልቅ ተስፋ የጣሉበት መሆኑንም ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ሮቤል ብርሃኑ፣ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን የሚገነባ አዋጭና ስልጡን አካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። በሀገራዊ ችግሮች ዙሪያ በአንድ ጣሪያ ሥር ምክክር ሲደረግ፣በመሠረታዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን ለመገንባት የሚያስችል ወሳኝ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በፖለቲካው መስክ መግባባትን በመፍጠር የሀገርን የኢኮኖሚ አቅም የሚገነባ የተረጋጋ የልማት ሥራን ለማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤም የኢኮኖሚ ዕድገትና የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክር የጋራ መግባባት የሚገነባ አዎንታዊ ምክረ ሐሳቦች የሚፈልቁበት እንደሚሆን ተስፋ አለኝ ብለዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ኃይሌ ዓለማየሁ በበኩላቸው፣ የአንድ ሀገር ዜጎች በጋራ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የምክክር ሐሳብ በመወጠን መሰባሰባቸው በራሱ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። ከዚህ ታሪካዊ መድረክ በኋላም የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያሳልጥ የጋራ መግባባትን በመገንባት፣ኢትዮጵያ በአፍሪካ ደረጃ መሪ ሀገር ለመሆን የሚያስችላትን አቅም እንደምትፈጥር እምነታቸውን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው አካታችነት በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን በመገንባት የሕዝብ አንድነትን ይበልጥ ያጠናክራል የሚል ተስፋ አለኝ ያሉት ደግሞ ያደታ ጉደታ ናቸው። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ አልማዝ ታምራት በበኩላቸው፣ የምክክር ጉባኤው በዜጎች መካከል ጠንካራ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት መሠረት የሚጥል የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የመዲናዋ ነዋሪ አስቻለው በርጋ እንዲሁ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የሚያግዝ ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል። አቶ ገረመው ደበበ በበኩላቸው፣ የሀገራዊ ምክክሩ ውጤትም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘላቂ ሰላምና የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የጋራ መግባባት ይፈጥራል የሚል እምነት አለኝ ብለዋል።
ማህበራዊ
የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን የሚያስችል አቅም ገንብቷል
Aug 11, 2026 72
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አደረጃጀትና አቅም መገንባቱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ። የቋሚ ኮሚቴው አባላት የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ጎብኝተዋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ባለፉት አምስት ዓመታት ኮሚሽኑ የተሰጠውን ኃላፊነት እንዲወጣ ላደረገው ድጋፍና ክትትል የምስጋና መርሃ-ግብር ተካሂዷል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኮሚሽኑ ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ ለውጦችን አስመዝግቧል። የኮሚሽኑን ሪፖርት ከመገምገም ባለፈም ቋሚ ኮሚቴው የመስክ ምልከታ በማድረግ ያልተቋረጠ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። የአደጋ ስጋት አመራር ፖሊሲን ከመከለስ ባለፈ የአዋጅ ማሻሻያ መደረጉን አንስተው፤ የተለያዩ ደንቦችም ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ ዜጎች ከተረጂነት አስተሳሰብ ተላቀው ወደ አምራችነት እንዲሸጋገሩ የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ ኮሚሽኑን በአዳዲስ አሰራሮችና በአዋጅ እንዲደራጅ በማድረግ በኢትዮጵያ ሊደርስ የሚችልን አደጋ አስቀድሞ መከላከልና ሲደርስ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እንዲገነባ ተደርጓል ብለዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ራዕዩን ማሳካት የሚያስችሉ ተስፋ ሰጭ ጥረቶችን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኮሚሽኑ ራስን በምግብ በመቻል የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት አከናውኗል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኮሚሽኑ ባለፉት አምስት ዓመታት ተጨባጭ ለውጦችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ ከለውጡ በኋላ በአዳዲስ አሰራሮችና ህጎችን በማሻሻል ሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን በራስ አቅም ማረጋገጥ የሚያስችል ውጤት አምጥቷል ብለዋል፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር የወባና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን የመከላከል ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል
Aug 11, 2026 96
ድሬደዋ፣ ነሃሴ 5/2018(ኢዜአ) ፡-በድሬዳዋ አስተዳደር የወባና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን የመከላከል ተግባር በተቀናጀ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉን የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ገለጸ። የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፅጌረዳ ክፍሌ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፤ አስተዳደሩ የወባና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን የመከላከል ተግባር በተቀናጀ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚህም የወባ እና የደንጊ ትኩሳት በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። በተለይ የወባ ትንኝ መራቢያ በሆኑ ቦታዎች ላይ የፀረ-ትንኝ ኬሚካል ርጭት በማካሄድና ውኃ ያቆሩ ስፍራዎችን በማጽዳት ረገድ ሰፊ የሕብረተሰብ ንቅናቄ ሥራ በመሥራት የአጎበር ስርጭት መካሄዱን ጠቁመዋል። በወባ በሽታ የሚያዙ ወገኖችም ፈጣን ሕክምና እንዲያገኙ ከመደረጉም በላይ፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ስለ በሽታው መከላከል የግንዛቤ ማስጨበጥና የቅኝት ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በአስተዳደር ደረጃ የወጣውን የጽዳት ሕግ በተቀናጀ መንገድ በመተግበር የወባና ተላላፊ በሽታዎችን ከመከላከል ባሻገር፣ ጽዱ ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ብለዋል። በተጨማሪም በገጠርና በከተማ በሚገኙ የጤና ተቋማት ወባን ከመከላከል ባሻገር፣ በተላላፊ በሽታዎች የተያዙ ሰዎችን አክሞ የማዳን ኃላፊነት በላቀ ዝግጁነትና ብቃት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
የዘላቂ የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን- የሃይማኖት አባቶች
Aug 11, 2026 91
ገንዳ ውኃ፤ ነሐሴ 5/ 2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን የዘላቂ የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድርሻቸውን እንደሚወጡ የሃይማኖት አባቶች ገለጹ። ይህ የተገለጸው "የሃይማኖት አባቶች ሚና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ" በሚል መሪ ሃሳብ በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ ነው። የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑት መልዓከ ኤዶም ማህቶት ማንደፍሮ፣ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በሚከናወኑ ተግባራት የሃይማኖት አባቶች የላቀ ሚናችንን በተደራጀ መልኩ መወጣት ይጠበቅብናል ብለዋል። በዚህም አብሮነትና ወንድማማችነት እንዲጠናከር የማድረግ ስራን አጠናክረን እንቀጥላለን በማለት አክለዋል። ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን በመገንዘብ፣ ማህበረሰቡ ከተሳሳቱ መረጃዎችና አሉባልታዎች ተጠብቆ፣ በእውነት ላይ የተመሠረተ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ በትብብር እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሌላኛው ተሳታፊ ሼክ ሙሐመድ አብዱልከሪም በበኩላቸው፣ "ህዝቡ እርስ በእርስ በመከባበርና በመደጋገፍ ለአካባቢው ሰላም መከበር የድርሻውን እንዲወጣ የማስተማርና የማንቃት ኃላፊነታችንን እንወጣለን" ብለዋል። መምህር ዳኘ አዲስ በበኩላቸው፣ "ለእውነተኛ ሰላም መስፈን በመቻቻል፣ በቅንነትና በወዳጅነት ተባብሮ መኖር ይገባል" በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ህዝቡ የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ ግዴታው እንደሆነ በመገንዘብ፣ የሃይማኖት ትምህርቶች በጥልቀትና በስፋት መስጠታችንን አጠናክረን መቀጠል ይገባናል ሲሉም አስገንዝበዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ ከንቲባ ተወካይ አቶ አዳነ ሀሰን፣ "የሃይማኖት አባቶች ሰላምን ለማስፈንና ማህበራዊ አብሮነትን ለማጠናከር እስካሁን ያደረጉትን በጎና ሚዛናዊ አስተዋጽኦ አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል" ብለዋል። ዘላቂ ሰላምን እውን ማድረግ የሚቻለው ማህበረሰቡን በእውነትና በደግነት መንገድ ላይ በመምራት መሆኑን ጠቅሰዋል። ሰላምን፣ መቻቻልን እና አብሮነትን በመስበክ ረገድ የእምነት አባቶች እያበረከቱት ያለውን ሚና አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ነው ያሉት። ህዝቡን ከከፋፋይ ንግግሮች፣ ከተሳሳቱ መረጃዎችና አሉባልታዎች በመጠበቅ፣ እውነትንና ፍቅርን መሰረት ያደረገ ግንዛቤ በማህበረሰቡ ዘንድ መፍጠር እንደሚጠበቅባቸውም አብራርተዋል።
በወላይታ ዞን ሰብዓዊ ድጋፎችን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Aug 11, 2026 105
ወላይታ ሶዶ ፤ ነሐሴ 5/2018(ኢዜአ)፦በወላይታ ዞን ለሚያጋጥሙ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽህፈት ቤት ገለጸ። የወላይታ ዞን አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ ሶርሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በወላይታ ዞን ለሚያጋጥሙ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በተለይም ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ሀብት የማሰባሰብና ሰብል የማምረት ሥራው ተጠናክሮ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ከ14 ሺህ 600 ኩንታል በላይ የእህል ክምችት መኖሩን ጠቁመው ምግብ ነክ ያልሆኑ ግብዓቶችም የድጋፍ ማሰባሰብ ተግባሩ አካል ሆነው እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ከ50 ሺህ ኩንታል በላይ የመያዝ አቅም ባላቸው ሁለት መጋዘኖች እህል የማከማቸት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው እስካሁን 184 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ እንደተቻለ ጠቁመዋል። የሀብት ማሰባሰቡም ሁሉንም አካላት በማሳተፍ እየተሠራ ነው ያሉት ኃላፊው እስከ ታህሣሥ 2019 ዓ.ም ባሉት ወራት 134 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በተጨማሪም በ2 ሺህ 500 ሄክታር ማሳ ላይ 200 ሺህ ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ በዘር የመሸፈን ሥራው በልዩ ትኩረት እየተሠራ መሆኑን አመልክተዋል። በዞኑ ባሉ 26 መዋቅሮችም ከ5 ሺህ ኩንታል በላይ የሚይዝ መጋዘን ተገንብቶ በተደራጀ መልኩ እህል የማሰባሰብና ሀብት የማከማቸት ተግባር እየተከናወነ ነው ብለዋል። የዞኑ ዳሞት ሶሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሉቀን መሸሻ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በወረዳው ለሰው ሠራሽና ለተፈጥሮ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ሥራ እየተሰራ ነው። ከወረዳው የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ጀምሮ የኅብረተሰቡን የመረዳዳት የቆየ ባህል ለማጎልበት በተከናወነ ተግባር፣ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡን ተናግረዋል። በወረዳው በተዘጋጀ መጋዘን እስካሁን ድረስ ከ1 ሺህ 500 ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡንና 30 ሄክታር መሬት በበቆሎ እየለማ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በወረዳው የሚከሰቱ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮችን በራስ አቅም ለመቋቋም፣ የአደጋ ሥጋትን መነሻ ያደረጉ የመከላከል ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ያሉት ደግሞ የዱጉና ፋንጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘካሪያስ ዎንታሞ ናቸው። ነዋሪውን፣ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ የሃይማኖት ተቋማትንና የሲቪክ ማኅበራትን በማሳተፍ ሀብትና እህል የማሰባሰብ ሥራ መጀመሩን ጠቁመዋል። እስከ አሁን ከ5 ሚሊዮን ብር በላይና ከ308 ኩንታል በላይ እህል መሰብሰቡን ተናግረዋል። ለዚሁ ዓላማ በመኸር ወቅት ለማምረት ከታቀደው 130 ሄክታር ማሳ ውስጥ 93 ሄክታሩ በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑንም አስረድተዋል።
ኢኮኖሚ
በምስራቅ ሸዋ ዞን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የግብርና ምርቶች ኤክስፖርትን ለማሳደግ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል
Aug 11, 2026 267
አዳማ፤ ነሐሴ 5/2018(ኢዜአ) ፡-በምስራቅ ሸዋ ዞን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የግብርና ምርቶች ኤክስፖርትን ለማሳደግ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ ገለፁ። የምስራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የዞኑ አመራሮች በቦሰት ወረዳ በኩታገጠም የለማውን የቦሎቄና በቆሎ ሰብል ያለበትንና የእንክብካቤ ሂደትን ጎብኝተዋል። አቶ አባቡ ዋቆ በወቅቱ እንዳሉት፤ በዞኑ በምግብ ራስን ለመቻልና የኤክስፖርት ምርቶችን ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት እየሰራን ነው። በዞኑ በ2018/19 የምርት ዘመን ከ580 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዋና ዋና ሰብሎች በቴክኖሎጂ በታገዘ አሰራር በዘር መሸፈኑን ለአብነት አንስተዋል። በተለይም በዘንድሮው ዓመት የአርሶአደሩን ምርትና ምርታማነት ለመጨመር የሜካናይዜሽን አገልግሎቱን በስፋት ለአርሶአደሩ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። አጠቃላይ በሰብል ከተሸፈነው የዞኑ መሬት ውስጥ ከ91 በመቶ በላይ በሜካናይዜሽን በመደገፍና ቴክኖሎጂን በመጠቀም በኩታገጠም የለማ መሆኑንም አንስተዋል። በዋናነት ከውጭ የሚገቡ የግብርና ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የኤክስፖርት ምርቶችን ለማሳደግ የተቀመጠውን ሀገራዊ ግብ እውን ለማድረግ በሚደረገው ሂደት ውስጥ የዞኑ ድርሻ የላቀ ነው ብለዋል። ለዚህም አርሶአደሩ ገበያ ተኮር ምርቶችን በተለይም ቦሎቄ፣ ማሾ፣ ሽንብራ እንዲሁም ስንዴን በስፋት በኩታገጠም እያለማ ይገኛል ብለዋል። በየደረጃው የሚገኙ የዞኑ አመራሮች በየዕለቱ በአርሶአደሩ ማሳ በመገኘት ቡቃያው የለበትን ሁኔታ በመመልከት በእንክብካቤው በተለይም በአረምና የሰብል በሽታን በመከላከል ላይ የተሟላ እገዛ ማድረግ የጉብኝቱ ዓላማ መሆኑንም ተናግረዋል። የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ መስፍን ተሾመ በበኩላቸው በዞኑ ከመደበኛው የሰብል ልማት በተጓዳኝ የግብርና ኤክስፖርት ምርቶች ላይ እየሰራን ነው ብለዋል። በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ88ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቦሎቄ በኩታገጠም መልማቱን ለአብነት አንስተዋል። ከዚህም ከሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ያሉት አቶ መስፍን፤ ከሚገኘው ምርትም 900 ሺህ ኩንታል ያህሉ ወደ ውጭ ይላካል ብለዋል። የኤክስፖርት ቦሎቄ ልማቱን አርሶአደሮቹ ከባለሀብቶች ጋር በኮንትራት እርሻ ውል እያለሙ መሆኑንም ገልጸዋል።
በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ማስፋፋት ሥራዎች ውጤታማነትን እያሳደጉ ነው
Aug 11, 2026 163
ቡታጅራ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ማስፋፋት ሥራዎች የኢንዱስትሪውን ውጤታማነት ይበልጥ እያሳደገው መሆኑ ተገለጸ። የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከ312 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ኢንዱስትሪዎች በቡታጅራ ከተማ ያስገነባቸውን የማምረቻ ሼዶች ዛሬ አስረክቧል። የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ናትናኤል ሚሊዮን በዚሁ ወቅት፣ ኮርፖሬሽኑ የአምራች ኢንዱስትሪውን ውጤታማነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል። በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶችን ከማበረታታት ባለፈ የመስሪያና የመሸጫ ሼዶችን ጨምሮ የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን በማስፋፋት ለሥራቸው ምቹ ሁኔታ እየፈጠረም ይገኛል። በዚህም በዘርፉ የተሰማሩ የግል ባለሀብቱን እና ሥራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ገልጸው፣ ከውጭ የሚገባ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካትም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬን ለማዳን ተችሏል ብለዋል። በዛሬው እለትም ከ312 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 7 አምራች ኢንዱስትሪዎች ስምንት ሼዶች የተላላፉ መሆኑን ገልጸው፣ ኢንዱስትሪዎቹ ከ 387 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል። አቶ ናትናኤል እንዳሉት፣ ኮርፖሬሽኑ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በተለያየ መንገድ በመደገፍ በዘርፉ እየተመዘገበ ያለውን ተጨባጭ ውጤት ለማስቀጠል የጀመረውን ሥራ ያጠናክራል። ዛሬ የማምረቻ ሼድ ከተላለፈላቸው ኢንዱስትሪዎች መካከል በዱራሜ ከተማ የከምባታ ቡና ማቀነባበሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሰልፊሶ በሰጡት አስተያየት ኢንዱስትሪው 150 ሚሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ መቋቋሙን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ከ150 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜአዊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ በኮርፖሬሽኑ የተመቻቸላቸው የማምረቻ ሼድ ለስራቸው ውጤታማነት አጋዥ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው በሀደሮ ከተማ በዝንጅብል ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራው የሱዳስ ግሩፕ ሥራ አስኪያጅ አቶ አስፋው አበበ በበኩላቸው ኢንዱስትሪው በ70 ሚሊዮን ብር የመነሻ ካፒታል ወደሥራ መግባቱን ተናግረዋል። ኢንዱስትሪው ለ100 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። የማምረቻ ሼዶችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማስተላለፍ በተዘጋጀው መርሐ ግብር ላይ የክልል ከፍተኛ አመራሮችና በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ተሳትፈዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል
Aug 11, 2026 202
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በግብርና፣ በአገልግሎት፣ በእንጨትና ብረታብረት እንዲሁም በሌሎች መስኮች የሥራ ዕድል በመፍጠር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተጀመሩ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል። ቢሮው በ2018 በጀት ዓመት በግብርና፣ በአገልግሎትና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ለ400 ሺህ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለመፍጠር አቅዶ ከ379 ሺህ 430 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለመፍጠር መቻሉን ተናግረዋል። የሥራ ዕድል ፈጠራውን ውጤታማ ለማድረግም በበጀት ዓመቱ ከ925 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ብደር መመቻቸቱን፣ 8 ሺህ 420 ሄክታር መሬት መቅረቡን እና 689 አዳዲስና ነባር ሼዶች ለኢንተርፕራይዞች እንዲተላለፉ መደረጉን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ የሥራ እድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ ነዋሪ ወጣት ዳዊት ትዛዙ እንዳለው ከመንግስት ባገኘው የገንዘብ ብድር በቅመማ ቅመም፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ መሰማራቱን ጠቁሟል። በአራት ሄክታር መሬት ላይ እያለማ ያለውን ቲማቲም ሽንኩርትና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመሩንም ተናግሯል። በአሁኑ ወቅትም ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ሥራ አጥ ወገኖች ጊዜያዊ ሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ገልጿል። በመንግስት ካገኘው የገንዘብ ብድር በተጨማሪ በተሰማራበት የእርሻ ሥራ ውጤታማ እንዲሆን በግብርና ባለሙያዎች ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግለትም ተናግሯል። ሌላው በሆሳዕና ከተማ ነዋሪ ወጣት ዳንኤል አሰፋ በበኩሉ በከተማው በሚገኘው ታዴ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ኢንተርፕራይዝ ቋሚ የሥራ ዕድል እንደተፈጠረለት ገልጿል። በዚህም በሚያገኘው ገቢ እራሱን ከማስተዳደሩ በተጨማሪ ነገ የራሱን ሥራ በመፍጠር ሕይወቱን የተሻለ ደረጃ ላይ ለማድረስ ራዕይ እንዲሰንቅ ማድረጉን ተናግሯል።
በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል
Aug 11, 2026 247
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ ህገወጥነትን በመከላከልና በማጋለጥ በኩል ህብረተሰቡ ተሳትፎውን ማጠናከር እንዳለበትም ጠቁመዋል። መንግሥት በተደራጀ ሙስናና ሕገወጥ ድርጊቶች የተሰማሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል የሕግ የበላይነትን እያረጋገጠ እንደሚገኝ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በሰጠው መግለጫ አሳውቋል፡፡ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት ከልማት ሥራዎች ባሻገር የሕግ የበላይነትን ማስፈን ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ የመንግሥትን ሕግ የማስከበር ርምጃ በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ የህዝብን ሀብት ከምዝብራና ብክነት መጠበቅ የመንግሥት ትኩረት ሊሆን ይገባል፡፡ በቅርቡ መንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊቶች ላይ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር በማዋል ተጠያቂነትን ለማስፈን የወሰደው እርምጃ ተገቢና ቀጣይነት ሊኖረው የሚገባ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጭዎች መካከል ሄኖክ ተስፋዬ፤ ርምጃዎቹ የሕግ የበላይነትን በማስፈን የመንግስትና የህዝብን ሀብት ከምዝበራ ማዳን ነው ብለዋል፡፡ በብልሹ አሰራርና ባልተገቡ አሰራሮች ላይ እየተወሰደ ያለው ርምጃ የመንግሥትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እና በዜጎች ዘንድ ደግሞ መተማመንን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ትዕግስት ገብረየስ፤ መንግሥት ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚወስደው ርምጃ እስከታች ባለው የመንግሥት መዋቅር ገቢራዊ መደረግ አለበት ብለዋል፡፡ መንግሥት ተጠያቂነትን ለማስፈን የጀመረው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በማንሳት፤ ሂደቱ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ወጣት ቴዲ ዑለማ በበኩሉ፤ መንግሥት የህግ የበላይነትን ለማስፈን የተግባር ቁርጠኛ መሆኑን ያሳየ ርምጃ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ሌላው አስተያየት ሰጪ አቢቲ ረጋሳ ሙስናና ብልሹ አሰራር የዕድገት ማነቆ መሆኑን በመግለጽ፤ ርምጃው አስተማሪና ትምህርት ሰጭ ነው ብለዋል፡፡ ማንም ሳይለፋና ሳይሰራ መበልጸግ የለበትም፤ ሙሰኞችን ለህግ ማቅረብ ተጠናክሮ መቀጠል ህዝቡም መተባበር አለበት ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በለጡ ዘላለም ናቸው፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Aug 11, 2026 202
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሂሚድ ገለጹ። 5ተኛው ዙር ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ የታዳጊዎች የስልጠና መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀምሯል። መርሃ ግብሩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሚያዘጋጀው ሲሆን በሳይበር ደህንነትና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ዝንባሌ ያላቸውን ታዳጊዎችና ወጣቶች ለማፍራት ያለመ ነው። የሳይበር ደህንነት፣ሶፍትዌር ልማት፣ኮዲንግ፣ አቪዬሽን፣የኤሮስፔስ ቴክኖሎጂ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች በመርሃ ግብሩ ተካተዋል። የሀርድ ዌር እና ሴኪዩሪቲ ዲዛይኖችን ማዘጋጀት የስልጠና መርሀ ግብር ሌላው የትኩረት ማዕከል ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር ውጤታማ ለማድረግ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው። ለዚህ ደግሞ በቁ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤አስተዳደሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሰው ሃይል የማፍራቱን ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል። የሰመር ካምፕ የስልጠና መርሃ ግብር የዚሁ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ ግብሩ የነገ የኢትዮጵያ ተስፋ የሆኑ ተተኪ ትውልድ በማፍራት ረገድ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ መጀመሩን አስታውሰው ፤ በአሁኑ ወቅት ስልጠናው በባህር ዳር፣ጅማ ፣ወላይታ ሶዶ፣ሀረማያ ዩንቨርስቲዎችን ጨምሮ በአስተዳደሩ ግቢ ውስጥ እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ የቴክኖሎጂ አቅሙ የተገነባ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የጀመረው ተተኪ ትውልድ የማፍራት ስራ የሚያስመሰግን ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለመርሃ ግብሩ ስኬት ዩንቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ድርሻ እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ሰልጣኞችም ኢትዮጵያን የማገልገል አደራ አለባቸሁ፤ለዚህ ደግሞ ስልጠናውን በአግባቡ ተከታትላችሁ ተገቢውን ክህሎት ልትጨብጡ ይገባል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል የመሶብ አገልግሎት የአፍሪካ ሀገራት በተሞክሮነት የሚጋሩት የመንግሥት አገልግሎቶች ማሳለጫ መሳሪያ ነው
Aug 10, 2026 631
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ዲጂታል የመሶብ አገልግሎት የአፍሪካ ሀገራት በተሞክሮነት የሚጋሩት የመንግሥት አገልግሎቶች ማሳለጫ መሳሪያ መሆኑን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ ገለጹ:: ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ በኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎት የሚሰጡ የአንድ ማዕከል፣ የተንቀሳቃሽና የተቀናጀ መሶብ ዲጂታል አገልግሎቶችን ጎብኝተዋል። የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ ዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል ፈጥሯል። ይህም ብልሹ አሠራርንና የመልካም አስተዳደር ውስንነቶችን በመቅረፍ፣ በመንግሥትና በዜጎች መካከል በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ያለው መተማመን እንዲጎለብት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የተበታተኑ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ማዕከልና በተቀናጀ አግባብ የሚመሩበትን ወሳኝ ዕድል በመፍጠር፣ የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ የተጀመረው የኢፌዴሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን ላይ በተንቀሳቃሽና በተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነቱ በእጅጉ መስፋፋቱን አስረድተዋል። የመሶብ አገልግሎትም የመንግሥት አገልግሎት ሥነ-ምኅዳር ውጤታማነትን በማሻሻል፣ እመርታዊ ውጤት እንዲመጣ እያደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የመሶብ ዋነኛ ዓላማ የዜጎችን የአገልግሎት እርካታ ማሳደግ መሆኑን በመጠቆም፣ ከመሶብ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ከ98 በመቶ በላይ የዜጎች የአገልግሎት እርካታ በማስመዝገብ ከፍተኛ ውጤት ማምጣቱን ጠቁመዋል። በቀጣይም በፌዴራል፣ በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች እየተስፋፋ የሚገኘውን የመሶብ አገልግሎት ተደራሽነት የበለጠ በማጠናከር፣ የዜጎችን አገልግሎት ለማሳለጥ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። በስምንት ተቋማት ከ40 በላይ አገልግሎቶች የተጀመረው የመሶብ አገልግሎት፣ በአሁኑ ወቅት በአንዱ ማዕከል ብቻ ከ27 በላይ ተቋማት የሚሰጡትን ከ288 በላይ አገልግሎቶች እያቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል። መሶብ ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ” ሽግግርን በማፋጠን፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የአገልግሎት ሥርዓት አካል ሆኖ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዲጂታል የመሶብ አገልግሎት ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በተሞክሮነት የሚቀስሙት የመንግሥት አገልግሎቶችን ማሳለጫ ተምሳሌታዊ አብነት መሆኑንም አስረድተዋል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የሀገራት አምባሳደሮችም፣ ኢትዮጵያ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያስመዘገበችውን እመርታዊ ውጤት፣ ልምድና ተሞክሮ እንዲቀስሙ ያለመ መሆኑን አንስተዋል። ይህም ዲፕሎማሲያዊ ትስስርን ለማጠናከር፣ ልምድ ለመለዋወጥና የትብብር ዕድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን አስረድተዋል። የመሶብ ሥራ ገና በመጀመሪያ ምዕራፍ ያለ ሲሆን፣ በቀጣይ የአገልግሎቶችን ቁጥር ማሳደግ፣ ዲጂታላይዜሽንን ማፋጠን፣ የመሶብ አገልግሎትን በሁሉም ከተሞችና ወረዳዎች ማስፋፋት እና ልምዱን ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ማካፈል ቀጣይ ትኩረቶች ይሆናሉ።
ወጣቶች ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እኩል መራመድ አለባቸው- የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ቤተልሔም ደሴ
Aug 10, 2026 156
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ ወጣቶች ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እኩል በመራመድ ራሳቸውን በክህሎት ብቁ እንዲያደርግ የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ቤተልሔም ደሴ ጥሪ አቀረበች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀረበውን የኢትዮጵያ ወጣቶች የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭን እንዲቀላቀሉ እና የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት የተሳታፊዎችን ቁጥር ወደ 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተደረገውን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት በኢኒሼቲቩ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በመቀጠል በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ልምዳቸውንና እይታቸውን ያካፈሉ አራት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። በ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ላይ ታሪኳን ያካፈለችው የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ቤተልሔም ደሴ፤ የቴክኖሎጂ ሕይወቷ ከአስራ ሰባት ዓመት በፊት ገና የአስር ዓመት ታዳጊ ባለችበት ወቅት እና የዲጂታል አማራጮች ጨርሶ በሌሉበት ሁኔታ ውስጥ እንደተጀመረ ገልጻለች። ያለፈውን ጊዜ ከአሁኑ ጋር በማነጻጸርም፣ ዛሬ ላይ ቴክኖሎጂ በስፋት ተደራሽ በመሆኑ የአሁኑ ዘመን ወጣቶች ህልማቸውን ለማሳካት የሚያስችል ምቹ መንገድ እንዳላቸው አመላክታለች። ይህ ትልቅ ዕድል ቢኖርም ስኬት ግን ፈጣን እርምጃን እንደሚጠይቅ ያስገነዘበችው ቤተልሔም፤ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመጠባበቅ ወጥተው አሁኑኑ የለውጥ መሪ እንዲሆኑ፣ እንዲሁም ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እኩል ለመራመድ ራሳቸውን በክህሎት በንቃት እንዲያበቁ ጥሪዋን አስተላልፋለች። ለተጨማሪ መረጃ እና ለመመዝገብ፦ ethiocoders.et #PMOEthiopia #DigitalEthiopia2030 #5MillionEthiopianCoders
ወጣት አዝመራው ታደሰ በኢትዮ ኮደርስ ኢኒሼቲቭ የስኬት ምዕራፍ
Aug 10, 2026 137
ወጣት አዝመራው ታደሰ የ 5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ተመራቂ ወጣት ባለሙያ ነው። ወጣቱ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ዙሪያ ባዘጋጀው የልምድ ልውውጥ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት ተሞክሮውን አካፍሏል፡፡ ወጣት አዝመራው በመርሐ ግብሩ ላይ እንዳለው ፥ ይህንን ታላቅ ዕድል በዩኒቨርሲቲ ቆይታው የመጨረሻ ዓመታት ውስጥ በመቀላቀል አስደናቂ የስኬት ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ወጣቱ ኮድ ማድረግን መማር ከጀመረበት ጥረት ተነስቶ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ኮደሮችን የሚያገናኝ ድረ ገጽ ወደ ማበልጸግ መሸጋገር መቻሉንና ዛሬ ደግሞ ፉል ስታክ ድረ ገጽ አልሚ መሆኑን አስረድቷል። በሰርተፍኬት ብቻ አትወሰኑ የሚለው ወጣት አዝመራው የተማራችሁትን በተግባር በማዋል እና በመለማመድ እውነተኛ ዕድገት ማምጣት ትችላላችሁ ሲል ተናግሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ሥዩም እንዳሉት ፥ የወጣቶች የቴክኒክና የዲጂታል ክህሎት ብቃት ወሳኝ ሀገራዊ ሀብት ነው፡፡ በዚህ ክረምት የኮደሮችን ቁጥር 7 ሚሊየን ለማድረስ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበውን ጥሪ ተግባራዊነት አረጋግጠዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር አባል ሆነች
Aug 10, 2026 639
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር (World Boxing) ባወጣው መረጃ መሰረት የማህበሩ ስራ አስፈፃሚ ቦርድ ኢትዮጵያን ጨምሮ የስድስት አገራትን የአባልነት ጥያቄ ማፅደቁን አሳውቋል። ይህንኑ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ እያሱ ወሰን ባስተላለፉት መልዕክት፣ ኢትዮጵያ ማህበሩን በመቀላቀሏ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። አክለውም፣ ይህ ለኢትዮጵያ የኩራት ጊዜ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ አንድ የአፍሪካ የቦክስ ቤተሰብ ለሁላችንም የደስታና የክብር ወቅት ነው ሲሉ ተናግረዋል። ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም በአፍሪካ ስፖርቱን የሚያጠናክር እያንዳንዱ እርምጃ ለሁሉም ድል መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህ ታሪካዊ ምዕራፍ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ሁሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ አዲሱ ምዕራፍ ለአፍሪካ ቦክስ ታላላቅ እድሎችንና ስኬቶችን ይዞ እንደሚመጣም ያላቸውን ምኞት መግለጻቸውን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ቻድ፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ላይቤሪያ፣ የመን እና ኩዌት ሌሎች የዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር አባል የሆኑ ሀገራት ናቸው። የዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር (World Boxing) የተቋቋመው እ.ኤ.አ. አፕሪል 2023 ነው። ማህበሩ በአዲስ መልክ የተቋቋመው የቀድሞው ዓለም አቀፍ የቦክስ ማህበር (IBA) የአሰራር እና የሙስና ችግሮች ስለነበሩበት፣ ቦክስ በኦሊምፒክ ስፖርትነት የመቀጠል እድሉን ለማስጠበቅ በሚል ዓላማ ነው። ዋና መስሪያ ቤቱን በስዊዘርላንድ ያደረገው የዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር (World Boxing) ዛሬ አባልነታቸው ተቀባይነት ያገኙትን ጨምሮ 168 አባል ሀገራት በስሩ ይዟል።
ለዋልያዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅት ለ39 ተጫዋቾች ጥሪ ቀረበ
Aug 10, 2026 622
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ለ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎች ለ39 ተጫዋቾች ዛሬ ጥሪ አድርገዋል። ጥሪ ከተደረገላቸው ተጫዋቾች መካከል ከ20 ዓመት በታች ናሽናል ካምፕ ላይ የሚገኙ ስድስት ተጫዋቾች ይገኙበታል። ተጫዋቾቹ አርብ ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በመሰባሰብ ዝግጅት ማድረግ እንዲጀምሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥሪ አቅርቧል። 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ በ2027 በኬንያ፣ ዩጋንዳ እና ታንዛንያ ጣምራ አዘጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ 24 ሀገራት ይሳተፋሉ። 48 ሀገራት በ12 ምድብ ተከፍለው ለአፍሪካ ዋንጫው ለማለፍ ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ በምድብ 10 ከሴኔጋል፣ ሞዛምቢክ እና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዎች በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም ይደረጋሉ።
ኢትዮጵያ በአለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና 6 ሜዳልያዎችን በማግኘት ውድድሯን አጠናቀቀች
Aug 10, 2026 217
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአሜሪካ ኦሪገን በተካሄደው የአለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና 6 ሜዳልያዎችን በማግኘት ውድድሯን አጠናቀቃላች። ትናንት እኩለ ሌሊት ላይ በተደረጉ የመጨረሻው ዕለት መርሃግብር በሁለቱም ፆታ በ1500 ሜትር ርቀት የተሳተፈችው ኢትዮጵያ ሜዳልያ ውስጥ መግባት አልቻለችም። በሴቶች ኤልሳቤት አማረ 4ኛ ፣ ሀረገወይን ካላዩ 9ኛ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።በወንዶች ደስታው ታዴ 12ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቅ ችሏል። ኢትዮጵያ በአጠቃላይ 2 ወርቅ ፣ 3 ብር እና 1 ነሐስ አሳክታለች። ከሁለት ዓመት በፊት በፔሩ ሊማ በተደረገው ተመሳሳይ ውድድር ኢትዮጵያ 6 የወርቅ ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ሜዳልያ በማግኘት ማጠናቀቋ ይታወሳል። የዘንድሮውን ውድድር አዘጋጇ አሜሪካ 24 ሜዳልያዎችን በመሰብሰብ በበላይነት አጠናቃለች። ኬንያ በ11 ሜዳልያ 2ኛ ሆናለች ፤ ኢትዮጵያ ከዓለም 5ኛ ከአፍሪካ ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን አጠናቃለች።
የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች የወጣቶችን ስብእና የመገንባት ሚና አላቸው
Aug 9, 2026 288
ደብረ ብርሃን፤ ነሐሴ 3/2018(ኢዜአ)፡-የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች የወጣቶችን ስብእና ለመገንባት ሚና እንዳላቸው የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ውድድርን ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ አስጀምሯል። የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ በዚህ ወቅት እንደገለጹት ከተማዋን የቱሪዝም፣ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማእከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። በተለይም የስፖርት ዘርፉን በማሳደግ ጤናማና አምራች ዜጋ ለማፍራትና በሀገር እና ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ወጣቶችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማ አስተዳደሩም ባለሀብቱንና ማህበረሰቡን በማስተባበር በየጊዜው የሚካሄዱ የታዳጊዎች ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድርን በልዩ ትኩረት እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል። በክረምት ወቅት ወጣቶች ገዜያቸውን የሚያሳልፉበትን ስፖርታዊ ውድድር ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ የተጀመረው ውድድርም የዚህ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ተክለዮሐንስ ኃይለጊዮርጊስ በበኩላቸው የክረምት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች ታዳጊዎች የእረፍት ጊዜያቸውን በአልባሌ ስፍራ እንዳያሳልፉ ለማድረግ ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። ዛሬ በተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች እግር ኳስ ውድድር በ60 ቡድኖች የታቀፉ 1ሺህ 500 ስፖርተኞችን በማሳተፍ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። የውድድሩ ዓላማ ወጣቶች በስፖርታዊ ስነ ምግባር ከመታነጽ ባለፈ ተሰጧቸውን አውጥተው በማሳየት በቀጣይ ለትልልቅ ክለቦች የሚመረጡበትን እድል የሚከፍት ነው ብለዋል። በተለይም ስፖርት ለሰላምና ለአንድነት ያለውን አበርክቶ በመጠቀም ወጣቶች አንድነታቸውን በማጠናከር ለአካባቢያቸው ሰላምና ልማት በጋራ እንዲሰለፉ ለማድረግ እንደሚካሄድ አስረድተዋል። "የኮኮብ እግር ኳስ ቡድን" አሰልጣኝ ሐብታሙ መለሰ፣ የክረምት ውድድር መዘጋጀቱ ታዳጊዎች በስልጠና ያገኙትን የቴክኒክ እውቀት በተግባር የሚያሳዩበት ዕድል ይፈጥርላቸዋል ብለዋል። "የአንድነት እግር ኳስ ቡድን" አሰልጣኝ ታምራት ደስታ በበኩላቸው ውድድሩ የባህል ልውውጥ በማድረግ አንድነትንና መተሳሰብን ለማጎልበት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል በደብረ ብርሃን ከተማ ዛሬ የተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ውድድር ለአንድ ወር የሚካሄድ መሆኑ ተመላክቷል።
አካባቢ ጥበቃ
ዩኒቨርሲቲው በብዝሃ ህይወት እና ዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ረገድ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች በምርምር እንዲፈቱ እያገዘ ነው
Aug 11, 2026 168
ሮቤ፤ ነሐሴ 5/2018(ኢዜአ)፡- የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በብዝሃ ህይወት እና ዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃና እንክብካቤ ረገድ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች በምርምር ተለይተው እንዲፈቱ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ከኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት የጎባ ቅርንጫፍ ጋር በመቀናጀት "ተስፋን እንትከል'' በሚል መሪ ሀሳብ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ዛሬ አካሄደዋል። የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬት በየጊዜው ከሚያደርገው ተሳትፎ በተጓዳኝ በዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ረገድ ሳይንሳዊ ምርምር እያካሄደ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው በተለይም በባሌ አካባቢ የሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን በሳይንሳዊ ምርምር የማገዝ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጾዋል። በዩኒቨርሲቲው የሚካሄዱት ምርምሮች፣ ከችግኝ ተከላ ጋር ተያይዘው በአየር ንብረትና በአካባቢ ላይ የሚደርሱ ችግሮችን በጥናት ለመለየትና መፍትሔ ለመስጠት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት የጎባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በንቲ ኦፍገሃ በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከዩኒቨርሲቲው ጋር በተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ዙሪያ ባለፉት ሦስት ዓመታት የተሰሩት ሥራዎች የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ገልጸው፤ በተለይም የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ በመደረጋቸው ጠፍተው የነበሩ የዱር እንስሳትና ምንጮች እየጎለበቱ መምጣታቸውን ጠቁመዋል። በችግኝ ተከላው ከተሳተፉ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት መካከል መምህር ኡመር መሐመድኑር፣ በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ እንደ ዜጋ በየዓመቱ ከመሳተፍ ባሻገር ችግኞቹ ፀድቀው ለውጤት እንዲበቁም የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ሥራው የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ለኢኮኖሚ ዕድገት መፍትሄ በሚሆን አግባብ መከናወን እንደሚገባውም እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በጎባ ክፍለ ከተማ ''ስራክ ጥብቅ ደን'' አካባቢ በተካሄደው መርሐ ግብር የደን፣ የመጠለያ፣ የእንስሳት መኖና ሌሎች ችግኞች መተከላቸውን ለማወቅ ተችሏል።
የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተከላ፣ክትትልና የፅድቀት መጠን በጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ እየተረጋገጠ ነው
Aug 10, 2026 182
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፦የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተከላ፣ ክትትልና የፅድቀት መጠን በጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ እየተረጋገጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በኢንስቲትዩቱ የካርታ ስራ መሪ ስራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ካሳሁን ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሳይንሳዊ የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ፣በጂፒኤስ (GPS) ልኬትና በሳተላይት ምስል ትንተና መደገፍ መጀመሩ በመረጃዎች ጥራትና በውጤታማነት በኩል ከፍተኛ ለውጥ አምጥቷል። የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ በዋናነት የመረጃዎችን የት፣እንዴት እና መቼ የሚሉ ሶስት መሰረታዊ ጥያቄዎች በትክክል መመለስ እንደሚረዳ ተናግረዋል። እንደ አቶ ቴዎድሮስ ማብራሪያ፣በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ችግኝ የሚተከልባቸው ቦታዎች በጂፒኤስ ንባብ አማካኝነት መጋጠሚያቸው ተለይቶ የተመዘገቡና ያልተመዘገቡ ተብለው ይከፈላሉ። በቅርቡ በተካሄደው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ከ291 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ሙሉ በሙሉ በጂፒኤስ ተለክቶና የቦታ ስፋቱ ተሰልቶ መደራጀቱን ጠቁመዋል። ይህ አሰራር ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ የመረጃ መደጋገሞችንና የመረጃዎች መሳሳትን ሙሉ በሙሉ ማስቀረቱን ገልፀዋል። አሁን ተግባራዊ በተደረገው አሰራር መረጃው ቢሮ እንደደረሰ በሳተላይት ምስል እንደሚረጋገጥ ጠቁመው፤ በተመረጡ ቦታዎች ላይ ባለሙያዎች በአካል በመገኘት የማረጋገጥ ስራ እንዲሰሩ ተደርጓል ብለዋል። ችግኝ መትከል ብቻውን ግብ አለመሆኑን በመግለጽ፣የተተከሉ ችግኞች ማደጋቸውንና የአካባቢውን አረንጓዴነት መለወጣቸውን ለመከታተል የርቀት ቴክኖሎጂ (Remote Sensing) ትንተና ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። ባለሙያዎች የደረቅ ወቅት የሳተላይት ምስሎችን በመጠቀም የመሬት ሽፋኑን (የከተማ፣ የእርሻ፣ የወንዝ እና የደን) የሪፍሌክታንስ (Reflectance) ዋጋ በመተንተን ትክክለኛውን የደን ሽፋን እንዲለዩ ይደረጋል ብለዋል። በዚህ ሳይንሳዊ መንገድ በተካሄደው ዳሰሳና በመስክ ማረጋገጫ ስራ፣ ቀደም ሲል 17 በመቶ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን በአሁኑ ወቅት ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማደጉ መረጋገጡን ገልጸዋል። ይህ ትልቅ ስኬት የተገኘው ህብረተሰቡ ባለፉት ስምንት ዓመታት ባደረገው ያልተቋረጠ ጥረትና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በተከናወኑ ስራዎች መሆኑንም አመላክተዋል። በአሁኑ ወቅት ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጃቸውን የደን፣ የሰብልና የከተማ መረጃ ክትትልን ጨምሮ 10 ማዕከላትን በመጠቀም መረጃዎችን ለውሳኔ ሰጪዎችና ለግብርና ሚኒስቴር ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል
Aug 8, 2026 177
ጂግጂጋ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል። 3ኛው ዙር የአካባቢ ብክለት መከላከል ክልል አቀፍ ንቅናቄ ''ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ'' በሚል መሪ ሐሳብ በጂግጂጋ ተካሄዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን እንደገለጹት፣ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል። ጽዱ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግም የፕላስቲክ ነክ ተረፈ ምርቶችን፣ የደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ብክለትን በመከላከል በውሃ እና አፈር ላይ እየተፈጠረ ያለውን ተጽዕኖ ለመቀነስ የወጡ ህጎችና መመሪያዎችን ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም የቆሻሻ ማስወገጃ ዘላቂ ሥርዓቶችን በመገንባት ከተሞች ምቹና ጽዱ እንዲሆኑ በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የአከባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በበኩላቸው፣ መርሃ ግብሩ ባለፉት ሁለት ዙሮች የተገኙ ውጤቶችን በማጠናከርና፣ በማስፋት፣ ጤናማና ንጹህ አካባቢን የመፍጠር ተግባሩን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን አመልከተዋል። ''እንዲሁም አካባቢያችንን ለመጠበቅ እና ለመጪው ትውልድ ፅዱ ኢትዮጵያን ለማውረስ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ለማረጋገጥም ጭምር ነው'' ብለዋል። 3ኛው ዙር የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በቀጣዮቹ ሶስት ወራት የሚተገበርና በዋናነት የፕላስቲክ ብክለትን በመከላከል፣ አደገኛ ኬሚካሎችንና ቆሻሻዎች አያያዝን፣ እንዲሁም የድምፅ ብክለትን የመከላከል ተግባራት እንደሚከናወንም አክለዋል። እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ ገለጻ፤ ፅዱ ኢትዮጵያ በመንግስት ብቻ የሚከወን ባለመሆኑ በየቤታችን፣ በየትምህርት ቤቱ፣ በየመሥሪያ ቤቱና በፋብሪካዎች የምንፈጽማቸው በጎ ተግባራት ተደምረው ትልቅ ሀገራዊ ለውጥ ያመጣሉ። በዚህም ሁሉም የመንግስት ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የሴቶችና የወጣቶች ማህበራት እንዲሁም እያንዳንዱ ዜጋ የዚህ ሀገራዊ ንቅናቄ ባለቤት በመሆን በንቃት እንዲሳተፍም ጥሪ አቅርበዋል። የሶማሌ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አስተዳድር ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ሙህየዲን አብዲ በበኩላቸው በክልሉ ባለፉት ዓመታት በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄዎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ጽዱ አካባቢ ለመፍጠር እየተከናወኑ የሚገኙ በርካታ ተግባራትም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የቢሮ ኃላፊው አረጋግጠዋል። በመርሃ ግብሩም በክልሉ ፕላስቲክን በመከላከል፣ መመሪያዎችን በመተግበርና ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ውጤታማ የሆኑ ከተሞች የእውቅና መስጠት ሥነ-ሥርዓት ተካሄዷል።
አረንጓዴ አሻራ ለትውልድ የሚተላለፍ ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ ባህል ነው
Aug 8, 2026 187
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያውያን ለትውልድ የሚያስተላልፉት ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ ባህል ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎት ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ሃላፊዎችና ሠራተኞች፣ ’’ተስፋን እንትከል’’ በሚል መሪ ቃል በእንጦጦ ሸገር ፓርክ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናውነዋል። የባንኩ የኮርፖሬት አገልግሎት ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ አረንጓዴ አሻራ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮችን መቋቋም ያስችላል። በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ስራዎች የታዩ ተጨባጭ ለውጦች መኖራቸውን አንስተው፣ በተለይም ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ስነ ምህዳሯ የተጠበቀና አረንጓዴ አገርን ለቀጣይ ትውልድ ለማስረከብ ችግኝ መትከልና መንከባከብ ወሳኝ ሀገራዊ ሀላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ባንኩ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ250 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን ገልጸው፤አረንጓዴ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ጠንካራ የኢትዮጵያዊያን የአካባቢ ጥበቃ ባህል መሆኑን ተናግረዋል። የባንኩ አመራሮች እና ሰራተኞችም በዚህ ታላቅ ሀገራዊ መርሀግብር የሚያደርጉትን ተሳትፎ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 491
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 511
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች። ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 799
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1282
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር!
Aug 9, 2026 474
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር! በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን ) የገጠሩ ማህበረሰብ የጨለማ ኑሮ የተፈረደበት ይመስል ኑሮውን ማሻሻል ሳይችል እልፍ ዓመታት ተቆጥረዋል፤ ለዘመናት መብራትና ውኃ ለማግኘትና ከቴክኖሎጂ ጋር ተቀራርቦ ለመኖር ወደ ከተማ መሰደድ ብቸኛው አማራጭም ነበር። የከተሜው ዋልታ የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት የሚወሰንበት የአራሹ ገበሬ የኑሮ ደረጃ ባህላዊውን የአኗኗር ዘዬ ባለመልቀቁ ደስተኛ ጊዜ የሚያሳልፍበት ሂደት አድካሚ እንደሚሆን ግልጽ ነው። የገጠሬው የተበታተነ የአኗኗር ሥርዓትም ለገጠሬው አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፤ የእዚህን የህብረተሰብ ክፍል ምርቱን እንጂ ኑሮውን የጠየቀ አልነበረም ቢባል ግነት አይሆንም። ቀደም ሲል በነበሩ መንግስታት ከተማን እንጂ ገጠርን ማዘመን የሚያስብ ስለመኖሩ ያጠራጥራል፤ ይህም በሀገሪቱ ለኢፍትሐዊ ዕድገት የራሱን ተጽዕኖ ሲያሳደር ቆይቷል። የመደመር መንግሥት ግን ይህን ቀይሮታል። ሀገር የመምራት ኃላፊነት ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ በከተማና በገጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ በዜጎች የኑሮ ሥርዓት ላይ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርጎ እየሰራ ነው ከተሜነት ብቻውን አድጎ የገጠሩ ማኅበረሰብ በቀድሞ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሆነ የተሟላ ዕድገት ማምጣት አይቻልም የሚል ጽኑ እምነት አለው። በእዚህም ከተማና ገጠርን ለማቀራረብ በገጠር ትራንስፎርሜሽንን የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ቀርጾ መተግበር ከጀመረ ከራርሟል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን አንዱ አካል የሆነው የገጠር ሞዴል መንደር በአርሶ አደሮች ዘንድ የሚጨበጥ ተስፋን ይዘው ከመጡ ኢኒሼቲቮች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። ከተስፋ ተሻግረው በዚህ ሞዴል መንደር የነዋሪነት ዕድልን ያገኙት ደግሞ ብርሃን አይተዋል፤ የትናት አኗኗራቸውን የቀየረ አዲስ ዛሬን በእጃቸው አድርገዋል፤ ነገን አልቀው መመልከት የግብርና ተግባራቸው አንዱ አካል ሆኗል። በአዲሱ መንደራቸው ዛሬ የሚያፈስ ቤት የለም፣ የእንስሳት ቆሻሻ ሽታ በአፍንጫቸው አይገባም፣ በሚቆረቁር እንጨት ወይም መደብ ላይ አይቀመጡም፤ የከተሜው መዘነጫ ሶፋ በሳሎናቸው ተከስቷል። ጓሮዎቻቸው ሁሉ ሙሉ እንደሆኑ አፍ አውጥተው የሚያወሩ ናቸው። በዚህ ቆስጣ፤ በዛ በኩል ጎመንና ቀይስር፤ ዘውር ሲሉ ደግሞ ከአስር የሚልቁ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፤ በአንድ ክፍል ደግሞ እናት ላም ከጥጃዋ ጋራ፣ የእንቁላል ዶሮ ከሥጋ ዶሮ ጋር ሁሉንም በአንድ ጊቢ ውስጥ ያገኛሉ። ምን ይሄ ብቻ አቮካዶ እና ፓፓያ፣ ሙዝና እንሰት፣ በርበሬና ሽንኩርት ሳይቀር ለተትረፈረፈ የአርሶ አደር ማዕድና ገበያ ራሳቸውን አዘጋጅተዋል። አርሶ አደር ኃይሉ ሞትንሞስ በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ ናቸው። እርሳቸው "መንግስት ጨለማችንን ገፎ ብርሃን አሳየን" ሲሉ በጠንካራ ቃላት የገጠር ሞዴል መንደር ፕሮጀክት ያመጣላቸውን በጎ ነገር ይገልጻሉ። እውነት ነው ያላዩትን ብዙ ነገር አሳይቷቸዋል። ያም ብርሃን ቤት ውስጥ የሚበራ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው፣ በነገ ተስፋቸውና በኢኮኖሚያቸው ላይ የፈነጠቀ ብርሃን ነው። ዛሬ ያሉበትን ህይወትም "ለእኔ አዲስ ነገር ነው። አይቼው አላውቅም፤ መቼም በራሴ ሀሳብ አላደርገውም ነበር።" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግስት አበራልኝ ያልኩት በእጄ ያለኝን ያላየሁትን ዕድል ስላሳየኝ ነው በማለትም ሀሳባቸውን ይቀጥላሉ። እኛ ሀብት አለን፤ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም። ይልቁንም የምናባክነው ይበዛል በማለትም የቀደመ ሕይወታቸውን እያሰቡ ይቆጫሉ። አሁን ግን ብዙ ተገነዘብኩ የሚያስብል የመደመር መንግስት በመኖሩ አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። እርግጥ ነው የገጠር ሞዴል መንደር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ነው። ለአብነትም የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ማንሳት ይቻላል። የተሠሩ ሞዴል መንደሮች በመጀመሪያ የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ የመሆን ዕድል ገጥሟቸዋል። በመቀጠል ንጽሕናው ያልተረጋገጠ የመጠጥ ውኃ ወንዝ ወርዶ ከመቅዳት ተቆጥበው በመንደራቸው የተገነባውን የከረሰ ምንድር ውሃ ከቧንቧ ቀድተው መጠጣት አስችሏቸዋል። በእሳት እና ኩራዝ ጭስ ሲሰቃዩ የነበሩ ዓይኖቻቸው ዛሬ ከሶላር ቴክኖሎጂ የመነጨ ብርሃን ማየት ጀምረዋል። ብርሃን ብቻ አይደለም ለወትሮ ለገበያ ወደ ከተማ ብቻ ሲወጡ ይመለከቱ የነበረውን ቴሌቪዥን ዛሬ በቤታቸው አስገብተው የመረጃና የመዝናኛ ዓለምን ተቀላቅለዋል። አርሶ አደሮቹ ቴሌቭዥንን ከመዝናኛነት ይበልጥ ለመረጃ እንደሚጠቀሙት ያነሳሉ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በዜና ተከታትሎ መረዳት፣ የገበያ ሁኔታን ማወቅ፣ የግብርና ሥራ ተሞክሮን መቅሰምና የአየር ንብረት ሁኔታን ጨምሮ ለሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙት ከቴሎቪዥን መስኮት እንደሆነ ይናገራሉ። በጓሯቸው የተትረፈረፈ የሌማት ትሩፋት ምርት መሰብሰብ የሚያስችላቸው ምቹ ሁኔታ ደግሞ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው። በተለይ መንግስት በጓሯቸው ጥምር እርሻ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የነገ ኢኮኖሚያቸውን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ ነው። ከተማን መናፈቅን ያስቀረው የገጠር ሞዴል መንደር ያኔ ከጅምሩ አመኔታን አላገኘም። የቦታና የአካባቢ ቁሳቁስ ለማቅረብ ዝግጁ እስካለመሆን የደረሱ አርሶ አደሮችም ነበሩ። በወቅቱ ጉዳዩን እንደፌዝ አዩት። ዛሬ ግን ውጤቱን በአግራሞት በዐይናቸው ተመለከቱ። የተናገረውን የሚከውን፤ የጀመረውን የሚጨርስ የመደመር መንግሥትን ተጨባጭ ስራዎች በማረጋገጥ እንደ ትንግርት ቆጠሩ። ዛሬ በየአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በቁጭት ተሞልተው መንደራቸውን ወደዚህ የሞዴል መንደር እሳቤ ለመቀየር ተነሳስተዋል። የጌሊት ቀበሌ አርሶ አደሮቹ መኮንን አርዶ እና ነጻነት ተስፋሁን ለዚህ ተጠቃሾች ናቸው። ያዩትን ተሞክሮ በራስ አቅም በመንደራቸው ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ከተማ ሄደን የምናወጣውን ወጪና የምናባክነውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት እዚሁ መዝናናት የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል። "ይህ ዕድል ለእኛ ለአርሶ አደሮች በታሪክ የሚነገር ትልቅ አጋጣሚ ነውም" ይላሉ። በጤዛ እየራስን እንጓዝበት የነበረው መንገዳችን ዛሬ ሰፍቷል። ተሽከርካሪ በደጃችን ስለሚያልፍም ምቹ ዕድልን ይዞልን መጥቷል። ይህን ጅምር ተግባር ወደ ላቀ ውጤት ማሸጋገር የእኛ ድርሻ ነውና ጠንክረን እንሠራለንም ብለዋል። ይህን ዕድል ወደ ትልቅ አቅም ለመቀየር መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ የሸሸቃ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር አልዓዛር ዘርክናንስ ናቸው። የዶሮና የከበት እርባታን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ ሥራን ከመደበኛው የእርሻ ሥራ ጋር አስተሳስረው በመሥራት ከቤተሰብ ፍጆታ ተርፎ ለገበያ የሚበቃ ምርት ለማምረት እየተዘጋጁ ነው። ይህም የገቢ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ልጆቻቸው ወተትና የወተት ተዋጽኦ በቤታቸው እንዲያገኙ ያደርጋል። ማር፣ እንቁላል እና ሥጋ እንዳያምራቸው የሚያደርግ ትልቅ ኢኒሼቲቭም ነው። አንዱ ቢጎድል በሌላው እየሞሉ የሚኖሩበትን የሥራ መስክ አጠናክረው ለውጤት አብቅተው ለተሻለ ለውጥ እንደሚሠሩ አክለዋል። የአርሶ አደር እናቶች ዘምቢል ይዘው አትክልትና ፍራፍሬ ሸመታ ወደ ገበያ ማቅናት የለባቸውም። ይልቁንም ከጎሮቸው ወደ ገበያ ይዞ መውጣት የኑሮ ዘዬያቸው ወግ ነው። ወይዘሮ መሠረት ማሞ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ያልለመዱትን አዲስ ሕይወት ከአዲስ ተስፋ ጋር መጀመራቸውን ከሚናገሩት መካከል ናቸው። ትናንት ኩሽናቸው፣ መኝታቸው እንዲሁም የከብትና የዶሮ ማደሪያ በአንድ ቤት ወስጥ የተወሰነ እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን ሽንት ቤትና መታጠቢያ ቤት ሳይቀር ለየብቻ የራሱ የሆነ ቤት ተገንብቶ ጽዳቱ የተጠበቀ ኑሮ መኖር ጀምረዋል። ቤታቸው ሲገቡና ሲወጡ ለዓይን ማራኪ፤ ለመቀመጥ ምቹ፤ ለመተኛትም ንጹህና ወገብ የሚያሳርፍ ሆኖ አግኝተዋል። እናም በዚህ እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። "መንግስት እንደ አባት ጎዶሏችንን ሞልቷል" ሲሉም ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ የአርሶ አደሮችን ሕይወት ብሩህ ያደረገው የገጠር ሞዴል መንደር ኢኒሼቲቭ በመላው ሀገሪቱ በመስፋፋት ላይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 16 ሞዴል መንደሮች በ16 ወረዳዎች ተገንብተዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ኢኒሺዬቲቩ የአርሶ አደር ኑሮ ዘዬን ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ጋር ለማቆራኘት ያስቻለ ነው። የተሻለ መኖሪያ ቤት ኖሮት በጓሮው የሚበላ ነገር ካጣ ሕይወቱ ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም። ይህም በመሆኑ ቤቶቹን ከእያንዳንዱ የግብርና ልማት ዘርፎች ጋር በማጣመር እንዲገነቡ የተደረገው። ይህም የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ስትራቴጂን የሚያጠናክርና ገበያን የማረጋጋት ዓላማን የያዘ ጭምር ነው። በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ የተገኘው መልካም ውጤት በቀጣይ በሁሉም ወረዳዎች የሚስፋፋ ሲሆን በዞን እና ወረዳ መዋቅሮች ድጋፍና ክትትል በቀበሌ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አንስተዋል። ይህ ኢኒሼቲቭ የሀገራዊ ብልጽግና ጉዞ አንዱ አቅም ነው። የተደመረ የማኅበረሰብ ብልጽግና ሀገርን ከፍ ያለ የዕድገት ማማ ላይ ያስቀምጣታል። እነሆ የክልሉ አርሶ አደሮች የአካባቢያቸውን ጸጋ ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ የሚቀይሩበት መስክ በሞዴል መንደር ምክንያት እጃቸው ላይ ደርሷል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉትም በብዙ መንገድ ጨለማ የከበበው የገጠሩ ማኅበረሰብ ሕይወት ዛሬ ብርሃን ማየት ጀምሯል። ይህ የብርሃን ፋና እየተቀጣጠለ ወደ ብዙኃኑ ሊደርስ የሁሉንም ፍላጎት አነሳስቷል። ሥሩ ከማለት ይልቅ ሠርቶ ማሳየትን የሚያስቀድመው የመደመር መንግስት የፈጠራቸው የገጠር ሞዴል መንደሮች ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን በዘላቂነት የሚያሳምሩ ናቸው። ሰላም እንሰንብት!
ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የአፍሪካ ኃያል ሀገር እየሆነች ነው-ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት
Aug 7, 2026 444
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት የመጪው ዘመን የአፍሪካ ኃያል ሀገር ወደመሆን እየተሸጋገረች ነው ሲል ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት ዘግቧል። ፈርስት ፖስት ሚዲያ ኢትዮጵያን በተመለከተ በሠራው ትንታኔው የሰው ዘር መገኛ፣የጥንታዊ መንግስታት ምድር፣የንግድ መስመሮች እና ከፍ ያለ የአፍሪካ ታሪካዊ መሰረት ያላት ሀገር መሆኗን አውስቷል። ሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ከቀድሞ ገናና ታሪኳ እኩል ታላቅ የሆነ አዲስ ምዕራፍ ለመገንባት በትጋት ላይ መሆኗን አንስቷል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት በቀጣናው እና የአፍሪካ ኃያል ሀገር መሆን የሚያስችላትን እንዲሁም የአህጉሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚበይንና የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሠራች መሆኗንም እንዲሁ። ለረጅም ዓመታት ዓለም ኢትዮጵያን የሚያውቃት በጦርነት፣በድርቅ እና በፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንደነበር በማስታወስ፥ዛሬ ግን ሀገሪቱ ይህንን የተዛባ ትርክት በኢነርጂ መሠረተ ልማት፣ በአቪየሽን፣ በማዕድን እና በዲጂታል ኢኮኖሚ አስደማሚ ለውጦች ለመቀየር እየሠራች ነው ብሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ተሻግራ እንዴት በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት ካላቸው ኢኮኖሚዎች ቀዳሚዋ ሆና ልትቀጥል ቻለች? የሚለውን ጥያቄ በማንሳትም በዝርዝር መልሶቹን ያብራራል። የዚህ ዋና ጥያቄ ዝርዝር ምላሽ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት እየተተገበሩ የሚገኙ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ ነው ያለው ሲል አንስቷል። • የመጀመሪያው የኢነርጂ አብዮት እና ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ነው። በዚህ የኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ጎልቶ የሚነሳው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሲሆን፣ ከ5 ሺህ ሜጋዋት በላይ የማመንጨት አቅም ያለው የአፍሪካ ትልቁ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት መሆኑን ፈርስት ፖስት በዘገባው ጠቅሷል። ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መሻቶች መሰረት፣የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የውጭ ምንዛሬ እና የቀጣናዊ ተጽዕኖ መፍጠሪያ አቅም መሆኑንም አብራርቷል። የሕዳሴ ግድብ ልዩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ከዓለም ባንክ ወይም ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አንድ ሳንቲም ሳይበደር በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም፣ ላብና ገንዘብ የተገነባ አፍሪካውያን በራሳቸው ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየነው ብሏል። ለኢትዮጵያውያን ግድቡ ከኮንክሪት እና ከተርባይን በላይ ትርጉም አለው ያለው ይህ የፈርስት ፖስት ዘገባ፥ እጅግ የላቀ እራስን የመቻል እና የኢኮኖሚ ነፃነት ማሳያ ሐውልት መሆኑንም ተንትኗል። ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን ለኬንያ፣ ለጂቡቲ እና ለሱዳን በመሸጥ ኤሌክትሪክን ወደ ከፍተኛ ገቢ ማመንጫነት እየቀየረች ከመሆኑም በላይ የመላው ምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የትስስር ማዕከል ሆናለች ነው ያለው። • የኢትዮጵያ የዕድገት ምሰሶ አቪዬሽን እና ቀጣናዊ ትስስር ኢነርጂ ብቻውን ኢኮኖሚያዊ አቅምን አይገነባም፤ ይልቁንም ኢነርጂ ኢንዱስትሪን ያነቃቃል፣ ትስስር ዓለም አቀፍ ንግድን ይመግባል ያለው ፈርስት ፖስት፥የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን ለላቀ የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ጉዞ መጀመሩን አንስቷል። በ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በየዓመቱ እስከ 110 ሚሊዮን ተጓዦችን እና ወደ 4 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ የዕቃ ጭነት ማስተናገድ አቅም አለው። ሙሉ በሙሉ ግንባታው ሲጠናቀቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከታላላቅ የአቪዬሽን ማዕከላት አንዱ ይሆናል ብሏል። ይህ ፕሮጀክት የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ መናኸሪያ የሆነችውን አዲስ አበባንና አፍሪካን፣ከሌሎች የዓለም ክፍሎች የሚያስተሳስር ዋና የመተላለፊያ ማዕከል እንደሚሆንም ተገልጿል። ስለዚህ አዲሱ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንት እና ለቱሪዝም፣ ለዓለም የዲፕሎሲ ትብብር ጉልህ ሚና እንዲያበረክት ታስቦ እየተገነባ ነው ብሏል። • የማዕድን ኢንቨስትመንትና በምግብ ራስን መቻል በሌላ በኩል ከኢትዮጵያ መሬት በታች ላለው የማዕድን ሀብቷ ትኩረት በመስጠት የልማት አብዮት እያካሄደች ስለመሆኑም ተንትኗል። ሀገሪቱ የወርቅና ሌሎች ማዕድናት ማውጫ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት አዳዲስ የውጭ ምንዛሬ ምንጮችን እያፈራች የማዕድን ኢንዱስትሪዋን እያሳደገች ነው። ወርቅ በፍጥነት ከኢትዮጵያ ቀዳሚ የወጪ ንግድ ምርቶች አንዱ በመሆን ለረጅም ጊዜ በግብርና ላይ ብቻ ጥገኛ ሆኖ የቆየውን ኢኮኖሚ ወደ ብዝኃ ዘርፍ እያሸጋገረ ይገኛል። በሌላ በኩል በምግብ ራስን ከመቻል ውጭ የትኛውም ኢኮኖሚያዊ ለውጥ የተሟላ ሊሆን አይችልም ያለው የፈረስት ፖስት ዘገባ፥ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆኑን ጠቅሷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን እንድትችል በጀመረው የለውጥ ጉዞ አስደማሚ ውጤት እያመጣ ነው ብሏል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከጉባ ብስራቶች አንዱ የሆነውና በሶማሌ ክልል እየተገነባ የሚገኘው የማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት በየዓመቱ 3 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ዩሪያ ማዳበሪያ ማምረት የሚችል ነው። ይህም ከውጭ የሚገባውን ማዳበሪያ ጥገኝነት በመቀነስ የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚያስችል አብራርቷል። "የምግብ ዋስትና የእኛ ስትራቴጂካዊ ጣልቃ ገብነት ነው።ያንን ግብ እውን ለማድረግ ግብአቶች ላይ መስራት አለብን።በግብአት ላይ መስራት ካልተቻለ የምግብ ዋስትናን እውን ለማድረግ መንገድ የለውም" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ በማካተት ዘገባው ሰፊ ሽፋን ሰጥቷል። ዲጂታላይዜሽን እና የኢንቨትመንትና የገበያ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ለውጥ ወደ ዲጂታልም እየተሸጋገረ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እንደተናገሩት የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠና ከዕቅዱ ቀድም ከመሳካቱም በላይ በርካታ ወጣቶች የዲጂታል እውቀት ባለቤት አድርጓል። በተመሳሳይ የዲጂታል ትስስር እየሰፋ ሲሆን የ4ጂ እና 5ጂ አገልግሎቶች በበርካታ ከተሞች ተደራሽ ሆኗል። ኢትዮጵያ ለበርካታ አስርት ዓመታት ተዘግተው የቆዩ እንደ ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ባንክ እና የካፒታል ገበያዎች ያሉ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጓንም አድንቋል። የካፒታል ገበያን መጀመሯም የግል ካፒታል ልውውጥን በማጎልበት ለኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተንትኗል። እነዚህ ማሻሻያዎች በአጠቃላይ በመንግስት ቁጥጥር ስር ከነበረው የኢኮኖሚ ወደ ግል ዘርፍ ኢንቨስትመንት እያደገ የሚሄድ ኢኮኖሚ መሰረታዊ ለውጥን እየተገነባ መሆኑን ያሳያሉ ነው ያለው። ኢትዮጵያ ካላት የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ አኳያ እድልና ፈተናዎች ከፊቷ መሆናቸውን በማንሳት፥ አዲሱን የዓለም አቀፍ የትብብር ጥምረት ብሪክስ አባል መሆኗን አውስቷል። ከቻይና፣ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት፣ ከምዕራባውያን አጋሮችና ከአፍሪካ ኢንቨስተሮች ኢንቨስትመንትን እየሳበች እንደምትገኝም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ጎራ ሳትለይ ከሁሉም የዓለም ሀገራት ጋር ትብብሯን እያጠናከረች ነው ብሏል። ዓለም ኢትዮጵያን የምታስታውሰው በጦርነት ቢሆንም፥ኢትዮጵያ ዓለም በአዲሱ የለውጥና የስኬት ጉዞዋ እንዲያስታውሳት እየሠራች ነው። ለዚህም በመላው ሀገሪቱ በሁሉም ዘርፍ ግዙፍ የኢኮኖሚ ሽግግር እየተካሄደ ሲሆን፥ ይህ የኢትዮጵያ ጉዞ ለቀጣዮቹ ዓመታት የቀጣናውንና የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊና አጠቃላይ ገጽታ በአዲስ መልኩ የሚቀርጽ ነው ሲል ፈርስት ፖስት ዘገባውን አብራርቷል።
ያቀደችውን በተግባር የምታሳካ ታላቅ ሀገር
Aug 3, 2026 758
የአንድ ሀገር ታላቅነት ከሚለካባቸው ጉዳዮች አንዱ የተያዙ ሀገራዊ እቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም ዋነኛው ነው። ኢትዮጵያም በዛሬው እለት በአንድ ጀምበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አዲስ ታሪካዊ ስኬት፣ ሀገሪቱ ያቀደችውን በተግባር ማሳየት የምትችልና ትልልቅ ህልሞችን የመተርጎም አቅም ያላት ታላቅ ሀገር መሆኗን ለመላው ዓለም በተግባር ያስመሰከረ ነው። ይህ በአንድ ጀምበር የተከናወነ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በርካታ ጥልቅ ትርጉሞችን የያዘ ነው፡ በአንድ ጀንበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ግዙፍ የሎጂስቲክስ፣ የዝግጅትና የህዝብ ንቅናቄ ስራን ይጠይቃል። ይህ ስኬት ሀገሪቱ ማንኛውንም ታላቅ አገራዊ እቅድ አቅዳ እስከ መጨረሻው የትግበራ ምዕራፍ ድረስ በብቃት የመምራትና የማስተባበር ተቋማዊና ህዝባዊ አቅም እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ዕድሜ፣ ጾታ፣ ወይም ልዩነት ሳይለያያቸው በአንድ ቀን ለተመሳሳይ አገራዊ ዓላማ መቆማቸው፣ ኢትዮጵያውያን ለጋራ እድገታቸውና ለሀገራቸው የወደፊት ተስፋ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትና አንድነት አሳይቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት ዋና ስጋት በሆነበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ እርምጃ ለችግሩ መፍትሔ በመስጠት ረገድ የዓለም አቀፍ መሪነቷን ያስመሰከረችበት አጋጣሚም ጭምር ነው። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የገጠሟትን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፈተናዎች ተሻግራ፣ አቅሟን አስተባብራ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ለዜጎቿም ሆነ ለውጭው ዓለም የሰጠችው ትልቅ የራስ መተማመንና የተስፋ መልእክት ነው። በአጠቃላይ፣ በአንድ ጀምበር የተከናወነው ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ አርቆ የማሰብና የማቀድ ችሎታዋን ብቻ ሳይሆን፣ ያቀደችውንም በአንድነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት በማውረድ በተግባር የምታሳይ ታላቅ ሀገር መሆኗን በግልጽ ያረጋገጠ አኩሪ ተግባር ነው።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ ትንሳኤ ብስራት!!
Aug 2, 2026 566
በሐዊ አጫሉ መግቢያ፡- የኢንዱስትሪ ዘርፍ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬን ከሚወስኑ ዋነኛ የብልፅግና ማረጋገጫ ምሰሶዎች መካከል በግምባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ዘርፉ ምርትን ከማሳደግ ባሻገር የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የሀገር ውስጥ ምርታማነትን የሚያፋጥን የልማት ሞተር ነው። ኢትዮጵያም ከግብርና መሠረት የተነሳ ኢኮኖሚዋን ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ሁሉን አቀፍ የምርት ሥርዓት ለማሸጋገር ከምታደርገው ጥረት መካከል ኢንዱስትሪውን በቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶነት በማካተት እየሰራችበት ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ አምስት ዐበይት የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት ምሰሶዎች ተመሥርቶ እየተመራ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥ ኢንዱስትሪው የምርት አቅምን በማሳደግ የግብርና ምርቶችን ወደ ተጨማሪ እሴት በመቀየርና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ እያስገኘ ነው። ይህንን ሽግግር እውን ለማድረግ የምርት አቅምን ማሳደግ፣ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር፣ የአቅርቦት ሰንሰለትን ማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና የሰው ኃይል ልማት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ የቀድሞ ገጽታ፤ ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ለውጥ መንገድ!! በቀደሙት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለያዩ ዕድሎችንና ፈተናዎችን በማስተናገድ በርካታ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል። ሀገሪቱን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር በተደረጉ ጥረቶች የተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተገንብተዋል። እነዚህ ፓርኮችም በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የተሞከረበት ወሳኝ ምዕራፍ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ ይህ ጉዞ በበቂ መሠረተ ልማት፣ በተሟላ የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና በተቀናጀ የምርት ሰንሰለት እጥረት ምክንያት በበርካታ ፈተናዎች ለመውደቅ ተገዶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ውስንነት፣ ዕውቅትና ክህሎትን የተሰላበሰ የሰው ኃይል አለመኖር፣ የፋይናንስ እጥረት፣ ውስብስብና አስቸጋሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትና የገበያ ትስስር እጥረት የዘርፉን እድገት ገድበው የነበሩ ሁነኛ ተግዳሮቶች ናቸው። ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ምርታማነት፤ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የለውጥ ፍኖት!! ባለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ ዘርፉ የተስተዋሉ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታትና የሀገሪቱን የማምረት አቅም ለማሳደግ አዳዲስ የለውጥ አቅጣጫዎች ተነድፈው ተተግበረዋል። በተለይም ኢንዱስትሪን ከተለመደው የምርት ሥርዓት በማሻገር ወደ ተወዳዳሪ ዘመናዊና ውጤታማ የማምረቻ ማዕከል ለመቀየር የተለያዩ የፖሊሲማሻሻያዎች ተደርገዋል። የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ፣ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን፣ የሰው ኃይል አቅምን ማሳደግና የግብርና-ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር በዘርፉ የተወሰዱ ሁነኛ የለውጥ እርምጃዎች ናቸው። በዚህም የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት በማጎልበት ከሀገር ውስጥ ገበያ እስከ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ድረስ ውጤት እያስገኘ ነው። የግል ባለሃብቱ ሚና፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሞተር!! የኢንዱስትሪ ልማት በመንግሥት ጥረት ብቻ የሚሳካ አይደለም። የግል ዘርፉ በካፒታል፣ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂና በአስተዳደር ብቃት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ለዘርፉ ዕድገት የማይተካ ሚና አለው። በዚህ ረገድ የግል ባለሃብቱ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዋና አጋር እንዲሆን የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተሻሽለው እየተሰራባቸው ይገኛል። ይህም የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት በማሻሻል፣ የንግድ ሥራ ሂደቶችን በማቀላጠፍ፣ የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋትና የምርት አቅምን በማሳደግ የግሉን ዘርፉ የምርታማነት አቅም እያጎለበተ ነው። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትንሳኤ ብስራት!! በሀገራችን የኢኮኖሚ አቅጣጫ ውስጥ የምርትና አገልግሎት አሰጣጥን በማቀናጀት አዲስ ምዕራፍ ከከፈቱ ዐበይት ሀገራዊ መርሃ-ግብሮች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተጠቃሽ ነው። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማምረት ባህልን በማሳደግ ዘርፉ ወደ አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚሸጋገርበት ሁነኛ ዕድልን ፈጥሯል። ንቅናቄው የማምረት አቅምን በማሳደግ ሥራ ያቆሙ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ መመለስ፣ የአምራቾችን ችግሮች በፍጥነት መፍታትና አዳዲስ ባለሃብቶችን ወደ ዘርፉ በመሳብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤ እያበረከተም ይገኛል። በዚህ ሂደት በፋይናንስ፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በውጭ ምንዛሬና በተቋማዊ ቅንጅት ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎች የአምራች ዘርፉን የምርታማነት አቅም በማጎልበት ጉልህ ሚና ተጫውቷል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲያንሰራራ በማድረግ የምርታማነት አብዮት እንዲቀጣጠል እያደረገ ይገኛል። የንቅናቄው ዋና ዓላማ በአምራች ዘርፉ የነበሩ ማነቆዎችን በመፍታት የኢትዮጵያን የማምረት አቅም ማሳደግ ነው። ይህም ሥራ ያቆሙ ወይም በአቅማቸው ልክ ያልሠሩ ፋብሪካዎችን ወደ ሙሉ ምርት በመመለስ የአምራቾችን ችግር በተቀናጀ መንገድ መፍታት፣ የፋይናንስና የግብዓት ተደራሽነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጓል። በዚህ ሂደት የማምረቻ ዘርፉ በአዲስ የሥራ ባህል፣ በተቋማዊ ቅንጅትና በፈጣን ውሳኔ አሰጣጥ እየተመራ መሆኑ የለውጡን ፍጥነት እያሳደገው ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ተደራሽነትን ማሻሻልና የምርት ጥራትን ማረጋገጥ የኢንዱስትሪው ትንሳኤ ዋና ማሳያዎች ናቸው። ለአብነትም፡- የፋይናንስ አቅምና የብድር አቅርቦት ማሻሻል፡- የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ እንቅፋት የሆነውን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ በተደረገው ርብርብ፣ የብድር አቅም ቀደም ሲል ከነበረበት 40 ቢሊዮን ብር ወደ 115 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ለአምራቾች ሰፊ የካፒታል አቅም መፍጠር ተችሏል። የውጭ ምንዛሬ ግኝትና የግብዓት ድጋፍ ማደግ፡- ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ይቀርብ የነበረው የውጭ ምንዛሬ መጠን አሁን ላይ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንዲደርስ ተደርጓል። ይህም ፋብሪካዎች ከአቅማቸው በታች እንዲሠሩ ያስገድድ የነበረውን የምርት ውስንነት በከፍተኛ ደረጃ አቃሎታል። የምርት ዕድገት፣ ተኪ ምርትና የኤክስፖርት አፈጻጸም፡- ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ ከነበረበት 348 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5.9 ቢሊዮን ዶላር በማደግ ግዙፍ ሀገራዊ ድል ተመዝግቧል። እንዲሁም በኤክስፖርት ገበያ የሚገኘው ገቢ ከ385 ሚሊዮን ዶላር ወደ 607 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ማለት ችሏል። ተቋማዊ ቅንጅትና አዲስ የሥራ ባህል ማዳበር፡- በክልሎችና በፌዴራል ተቋማት መካከል የነበረውን የቢሮክራሲ ጫና በመቀነስ ፈጣን ውሳኔዎች እንዲሰጡ መደረጉ፤ እንዲሁም ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርትን በኩራት የመጠቀም እና የሀገር ፍቅር ስሜትን ከአምራችነት ጋር የማስተሳሰር ትልቅ ማህበራዊ ንቃተ-ህሊና መገንባት ተችሏል። የወደፊት ተስፋ፤ ኢትዮጵያ አዲሲቷ አፍሪካዊት የኢንዱስትሪ ምርታማነት ተምሳሌት ሀገር!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ በቀጣይ ዓመታት ከተለመደው ማምረት ወደ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ሥርዓት እንዲሸጋገር ይጠበቃል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሜሽን፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና የፈጠራ ሥርዓቶችን ወደ ማምረቻ ዘርፉ ማስገባት የወደፊቱ ትኩረት ይሆናል። በተመሳሳይም ጠንካራ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስር፣ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት፣ ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአህጉራዊ ገበያ ተደራሽነት የሀገሪቱ ቀጣይ የኢንዱስትሪ ግቦች ናቸው። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) የሚፈጥረውን ሰፊ የገበያ ዕድል በመጠቀም ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችል መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ማጠቃለያ፡- ማምረት፤ የኢትዮጵያ የብልፅግና ቁልፍ መሳሪያ!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ተጨማሪ እሴት ያለው ምርት አቅራቢነት በማምራት እመርታዊ ውጤቶችን እያስገኘ ነው። የኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ማለት ፋብሪካዎችን ብቻ ማስፋፋት ሳይሆን የሀገርን ምርታማነት፣ የወጣቶችን ዕድል፣ የኢኮኖሚ ነፃነትንና የልማት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን የዛሬ ልማት ብቻ ሳይሆን የነገውን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚገነባ ሀገራዊ ራዕይ ነው።
ትንታኔዎች
ወዳጅነት ፓርክ ፦ የመደመር እሴት ማሳያ
Aug 11, 2026 97
በሙሴ መለሰ በአዲስ አበባ መሐል የሚገኘው የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት ስምንት ዓመታት ከተገነቡት የመጀመሪያዎቹ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች አንዱ ነው። ይህ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውና 56 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ባለው የ“ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት” (Beautifying Sheger Project) ስር የተከናወነ ነው። ፕሮጀክቱ በሁለት ዋና ዋና ምዕራፎች ተከፍሎ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ሊጠናቀቅ ችሏል። ኢትዮጵያ የጀመረችው ይህ የከተማ ውበትና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ የውበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ሀብት ፈጣሪ መሆኑንም በተግባር ያረጋገጠ ህያው ማሳያ ነው። የወዳጅነት አደባባይ የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሂደት በ2011 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የቆሻሻ ማጠራቀሚያና ክፍት ቦታ የነበረውን ስፍራ ወደ ዘመናዊ አረንጓዴ ሥነ-ምህዳር ለመቀየር ያለመ ነበር። ግንባታው በ11 ወራት ብቻ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ በጳጉሜ 2012 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በቀድሞዋ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል። ይህ ክፍል 32 ሄክታር መሬት በማልማት፣ አሳ እና ዳክዬዎች የሚቀዝፉበት ሰው ሠራሽ ሐይቅ፣ ትልቅ አደባባይ (Square)፣ እና 1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻን መልሶ ማቋቋምን ያካተተ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ለምሽት መዝናኛ የሚሆን ማራኪ የፏፏቴ ላይ የብርሃን ትርኢት (Dancing Fountain)፣ ከ16 በላይ የውጪ ላይ ስብሰባ ማካሄጃ ቦታዎች (Event Venues)፣ የሰርግ አፀዶች፣ ካፌዎች፣ የፎቶ ስቱዲዮዎች እና ጠዋት ጠዋት የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ሩጫ ለማድረግ ምቹ የሆኑ የተከለሉ መንገዶችን ይዟል። ምዕራፍ አንድ ከተመረቀ በኋላ ወዲያውኑ የሁለተኛው ምዕራፍ (Friendship Park 2) የዲዛይንና የዝግጅት ሥራዎች ተጀምረዋል። በግንባታው ወቅት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም፣ ከሌላ ቦታ የተሰባሰቡ ከ4ሺህ በላይ አገር በቀል ትልልቅ ዛፎች (Indigenous trees) መጥተው በቦታው ላይ በተሳካ ሁኔታ እንዲተከሉ ተደርጓል። ግንባታው በጥቅምት 2015 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተመርቋል። 16 ሄክታር መሬት የሸፈነው ይህ ክፍል ከአብርሆት ቤተ-መጽሐፍት ፊት ለፊት የሚገኝ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ለሕፃናት፣ ለታዳጊዎችና ለቤተሰብ ስፖርታዊ መስተጋብር ተለይቶ የተገነባ ነው። በውስጡም እጅግ ዘመናዊና ሰፊ የሕፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን (Playgrounds)፣ ታዳጊዎች እየተጫወቱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን የሚለማመዱበትን የሳይንስ ማዕከል፣ ትንንሽ የእግር ኳስ (Mini-football) እና የቅርጫት ኳስ (Basketball) ሜዳዎችን፣ የሩጫ ትራኮችን፣ ለወጣቶች ንባብ የሚሆኑ ቦታዎችን (Reading nooks) እና ከጎኑ ያለውን የሳይንስ ሙዚየም ግንባታን ያካተተ ሰፊ ይዘት አለው። የወዳጅነት ፓርክ ከብሔራዊ ቤተመንግሥት እስከ መስቀል አደባባይባለው አካባቢ የሚዘልቅ ዘመናዊ የሕዝብ መገልገያና መዝናኛ ማዕከል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ ይህ ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ ማስገኘት ችሏል። ይህም የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ራሳቸውን ችለው ከፍተኛ ገቢ ማመንጨት ከመቻል ባለፈ፣ በቱሪዝም ዘርፉ፣ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዘንድ ለበርካታ ዜጎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሰፊ የሥራ ዕድል እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እየፈጠረ ይገኛል። ከዚህ ኢኮኖሚያዊ እሴቱ ባሻገር፣ ፕሮጀክቱ የከተማ ነዋሪዎችን ማኅበራዊ ትስስር በከፍተኛ ደረጃ ያጠናክራል፤ የዜጎችን የኑሮ ጥራት፣ የጤና ሁናቴ እና ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ (Life style) ከማሻሻል አንጻርም የመደመር እሴት በተግባር መሬት ማወረዱንና የዜጎችን አገራዊ የባለቤትነት ስሜት በጽኑ የሚያሳድግ ትልቅ ማሳያ ነው። ፓርኩ ለጤና፣ ለአካል ብቃት፣ ለመዝናኛና ለንባብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ወጣቶች ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን በስፖርት፣ በዕውቀት ቀሰማና በሌሎች በጎ ነገሮች ላይ እንዲያሳልፉ ምቹ ከባቢ ፈጥሯል። በተጨማሪም ቦታው ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎችና ጎብኝዎች በየቀኑ በስፋት የሚገናኙበት ማዕከል መሆን ችሏል። በስፍራው ከቤተሰቦችና ሕፃናት፣ ከስፖርት ቡድኖችና ከሠርግ ተካፋዮች ጀምሮ እስከ ዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎች በከፍተኛ ቁጥር ይገኙበታል። ይህም ለሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች (Content Creators) ምቹ ከባቢ በመፍጠር፣ የአዲስ አበባን ዘመናዊና ማራኪ ገጽታ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት እንዲያስተዋውቁና የከተማዋን በጎ ስም ለዓለም እንዲያደርሱ ትልቅ ዕድል ከፍቷል። ይህ ፓርክ አዲስ አበባን ለሌሎች የክልል ከተሞች በአረንጓዴ ልማት፣ በጽዳትና በዘመናዊ የሕዝብ መገልገያዎች በሞዴልነት የሚጠቀስ ሲሆን፣ የከተማዋን የዲፕሎማሲያዊ መዲናነት ገጽታ ይበልጥ በማደስ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች፣ ለዲፕሎማቶችና ለዓለም አቀፍ እንግዶች በጣም ሳቢና ተመራጭ መዳረሻ አድርጓታል። ፓርኩ በከተማዋ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ውስጥ እየተገነቡ ላሉ ተመሳሳይ የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ቀዳሚ ማሳያ ሲሆን፣ እነዚህ አዳዲስ ቦታዎች እሴት የሚፈጥሩ፣ ዕድሎችን የሚያመቻቹ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያንን ባለቤትነት የሚያረጋግጡ ማዕከላት መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ያረጋግጣል።
የኮደሮች ኢኒሼቲቭ፡ የኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታና የወጣቶች ብሩህ መፃኢ ዕድል
Aug 10, 2026 131
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በዲጂታሉ ዓለም ያላትን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እና የወጣቶችን ክህሎት ለማልማት ያለመው የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ተጀምሯል። ይህ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች መካከል በተደረገ ትብብር የተዘጋጀ ሀገራዊ የዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ ፕሮጀክት ነው። ዋና ዓላማውም ወጣቶች በዲጂታሉ ዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆኑና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈለጉ የቴክኖሎጂ ክህሎቶችን እንዲጨብጡ ማስቻል ነው። የስልጠናው መርሃ ግብር በኦንላይን ”Udacity” በተሰኘ ዓለም የትምህርት መድረክ በኩል የሚሰጥ ሲሆን፣ በዌብ ዲቨሎፕመንት፣ በዳታ አናሊቲክስ እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዋና ዋና ዘርፎች የተከፈለ ነው። ከእነዚህም ጎን ለጎን የንግድና ሥራ ፈጠራ እንዲሁም የመሪነት ክህሎት አጫጭር ስልጠናዎች ተካተዋል። እያንዳንዱ ኮርስ በግል ፍጥነት የሚወሰድ ሆኖ በአማካይ ከ6 እስከ 7 ሳምንታት የሚወስድ ሲሆን፣ ስልጠናውን በጥሩ ሁኔታ ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ሙሉ በሙሉ በነፃ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው የ’Udacity’ እና የኢኒሼቲቩ ይፋዊ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ይሰጣል። በዚህ ፕሮግራም ላይ ዕድሜው ከ13 ዓመት በላይ የሆነ ማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ የቀደመ የኮዲንግ እውቀት ሳይጠይቀው መመዝገብ ይችላል። ለመማር የሚያስፈልጉት ነገሮች የኢንተርኔት ግንኙነት ያለው ኮምፒውተር ወይም ስማርትፎን ብቻ ሲሆኑ፣ ምዝገባውም በይፋዊው 5millioncoders.gov.et ድህረ ገጽ በኩል ይከናወናል። የኢኒሼቲቩ የመጨረሻ ግቦች ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ እና በመላው አህጉር ውስጥ የቴክኖሎጂ ማዕከል ማድረግ እና የዲጂታል ስትራቴጂዎችን ማሳካት ናቸው። በተጨማሪም ሰልጣኞች በሀገር ውስጥና በውጭ ድርጅቶች እንዲቀጠሩ፣ ከቤት ሳይወጡ በዶላር የሚከፍሉ የርቀት ስራዎችን እንዲሰሩ እና የራሳቸውን የቴክኖሎጂ ስታርታፕ እንዲመሰርቱ መንገድ ይከፍታል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ የሚታየውን የክህሎት እጥረት በመሙላትና ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ገቢ በማስገኘት የወጣቶችን ተወዳዳሪነትና በራስ የመተማመን አቅም ያሳድጋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት ሀገራዊ ጥሪ፣ ይህ ክረምት በከንቱ እንዲያልፍ ሳይፈቀድ ወጣቶች በነጻ የሚሰጠውንና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለውን ትምህርት እንዲወስዱ አሳስበዋል። አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ቀድመው የወሰኑ በመሆናቸው፣ ሌሎችም ይህንን እድል በመጠቀም የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት የተሳታፊዎችን ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ለማድረስ የቀረበውን ጥሪ እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል። ይህንን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል። ዝግጅቱ የዘርፉን መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጭዎችን፣ የምስክር ወረቀት ያላቸውን የኢኒሼቲቩን ተመራቂዎች እና ወጣት ባለሙያዎችን በአንድነት ያገናኘ ሲሆን፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ ባተኮረ የኤግዚቢሽን ጉብኝት ተጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ሥዩም የመክፈቻ ንግግር ቀጥሏል። ኃላፊዋ የወጣቶች የቴክኒክና የዲጂታል ክህሎት ብቃት ወሳኝ ሀገራዊ ሀብት መሆኑን ገልጸው፣ የኮደሮችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የቀረበውን ጥሪ ተግባራዊነት አረጋግጠዋል። ቀጥሎ በተካሄደው የፓናል ውይይት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር አብዮት ባዩ፣ የጊሮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቤተልሔም ደሴ፣ እንዲሁም የኢኒሼቲቩ ምሩቃን የሆኑት አዝመራው ታደሰ እና የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ማኅሌት ሥዩም ልምዳቸውንና እይታቸውን አካፍለዋል። ፓናሊስቶቹ ወጣቶች ክህሎታቸውን ያለማቋረጥ እንዲያሳድጉ እና በኢትዮጵያ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር ዕድገት ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ያበረታቱ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩም የኢኒሼቲቩን ከፍተኛ ሀገራዊ ሚና በድጋሚ ያረጋገጠ ሆኖ ማለፉን ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያላትን ራዕይ ለማሳካት የተጣለ ትልቅ መሰረት ነው። ወጣቶች በቴክኖሎጂው ዘርፍ የሚጨብጡት ዕውቀት የራሳቸውን የፈጠራ መንገድ ከመክፈቱም በላይ፣ ሀገሪቱ በምስራቅ አፍሪካና በአህጉሪቱ የቴክኖሎጂ ማዕከል ሆና እንድትወጣ ያስችላታል። በመሆኑም ይህን አጋጣሚ በአግባቡ መጠቀም ለሀገሪቱ ዘላቂ እድገትና ለወጣቱ ብሩህ ተስፋ ወሳኝ እርምጃ ነው።
የአፍሪካ የውሃ ማማ ኢትዮጵያ ሳትሆን ግብፅ ናት!
Aug 10, 2026 334
ግብጽ ራሷን የምትስልበት የውሃ እጥረት ትረካ ከነባራዊ ሁኔታም በእጅጉ የተቃረነ ነው። የአፍሪካን የታሪክ፣ የኢኮኖሚና ጂኦ-ፖለቲካ በከፍተኛ ሁኔታ ከሚቃኙት ተፈጥሯዊ ሃብቶች መካከል ውሃ ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይይዛል። አፍሪካውያን የውሃ ሀብታቸውን በጋራ አልምቶ የመጠቀም ፍላጎታቸውና ጥረታቸው የአህጉሪቱን የወደፊት የልማትና የሰላም አቅጣጫ የሚወስን ወሳኝ ጉዳይ ቢሆንም ይህ አህጉራዊ የትብብርና የጋራ እድገት መንፈስ እውን ሊሆን የሚችለው የተፋሰሱ ሀገራት ያላቸውን እውነተኛ የውሃ ሀብት መጠንና ፍላጎት በሳይንሳዊ እውነታዎችና በግልጽኝነት ላይ ተመስረተው ሲተገብሩት ብቻ ነው። በዚህ አህጉራዊ የተፋሰስ ትብብር ውስጥ ትልቁን ስፍራ የሚይዘው የታላቁ ዓባይ ወንዝ ተፋሰስ ነው። ሆኖም ለዘመናት የዘለቀውና አሁንም ድረስ በዲፕሎማሲው መድረክ የሚንጸባረቀው ዋነኛው ማነቆ ግብፅ እራሷን "ለከፍተኛ የውሃ እጥረት የተጋለጠችና ፍጹም የዓባይ ጥገኛ የሆነች ብቸኛ ሀገር" አድርጋ የምታቀርብበት ትርክት ነው። ይህ ትረካ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብን ሲያደናግር ቆይቷል። ነገር ግን የጂኦግራፊ፣ የሃይድሮሎጂና የዘመናዊ ቴክኖሎጂ መረጃዎችን በጥልቀት ስንመረምር ግብፅ እራሷን የምትስልበት የውሃ እጥረት ትረካ ከእውነተኛው ነባራዊ ሁኔታ ጋር በእጅጉ የሚቃረን ሆኖ እንገኘዋለን። ግብፅ በውስጧ የያዘቻቸውን ግዙፍና ያልተነኩ ድብቅ ሀብቶች፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን እና በበረሃ ውስጥ የምታከናውናቸውን ሰፋፊ የውሃ ማዞር ፕሮጀክቶች ስንመለከት ሀገሪቱ እውነተኛ የውሃ እጥረት ሳይሆን ከፍተኛ የውሃ ሀብት ያላት መሆኗን በግልጽ ያሳያል። ይህንን እውነታ በግልጽ የሚያስረዱትንና የግብፅን እውነተኛ የውሃ ማማነት የሚያረጋግጡትን ዋና ዋና ሳይንሳዊና ተግባራዊ ማስረጃዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦ የከርሰ ምድር ውሃ ከገፀ-ምድር ውሃ ባሻገር በግብፅ፣ ሊቢያ፣ ሱዳን እና ቻድ ስር የሚገኘው የኑቢያ አሸዋማ ድንጋይ የከርሰ-ምድር ውሃ ስርዓት (Nubian Sandstone Aquifer System) በዓለም ላይ ካሉ የከርሰ-ምድር ውሃዎች ትልቁ ነው። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት በግብፅ ግዛት ስር ብቻ የሚገኘው የዚህ ውሃ መጠን ከ5 ትሪሊዮን እስከ 10 ትሪሊዮን ኪዩቢክ ሜትር እንደሆነ ይገመታል። ይህ ግዙፍ ሀብት የዓባይ ወንዝን የአምስት ክፍለ-ዘመናት (500 ዓመታት) አጠቃላይ የውሃ ፍሰት የሚበልጥ ድብቅ ሃብት ነው። ግብፅ ይህንን ሀብቷን በዘመናዊ መንገድ አውጥታ ብትጠቀም ለበርካታ አስርት ዓመታት ያለ ምንም የገፀ-ምድር ውሃ ስጋት መኖር የሚያስችላት ስትራቴጂካዊ ክማቸት አላት ማለት ነው። የአስዋን ከፍተኛ ግድብና የናስር ኃይቅ የግብፅ የውሃ መከላከያ ማዕከል የሆነውና በአስዋን ከፍተኛ ግድብ የተገደበው ናስር ሀይቅ እስከ 169 ቢሊዮን ኩቢክ ሜትር ውሃ የመያዝ አቅም አለው። ይህም ማለት በናስር ሃይቅ የተከማቸው ውሃ ብቻ የግብፅን የዓመታት ሙሉ የውሃ ፍላጎት ያለ ምንም ተጨማሪ የወንዝ ፍሰት መሸፈን የሚያስችል ግዙፍ ስትራቴጂካዊ መያዣ (Buffer) ሆኖ ያገለግላል። የባሕር ውሃ ማጣራት አቅምና የግብጽ 2050 ማስተር ፕላን ግብፅ በሜዲትራኒያን እና በቀይ ባህር ረጅም የባህር ዳርቻዎች ያሏት በመሆኑ በጨዋማ ውሃ ማጣሪያ ቴክኖሎጂ ትልቅ እርምጃ እየወሰደች ትገኛለች። በአሁኑ ወቅት በቀን ከ1 ነጥብ 5 እስከ 2 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተጣራ ውሃ እያመረተች ሲሆን፤ በግልና በሕዝብ ፣ በካርቦን ቅነሳ ድጋፎች እና በባህር ዳርቻ ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች አማካኝነት የማጣራት አቅሟን በጥሬው በእጥፍ ለማሳደግ የሚያስችል እስከ 2050 የሚዘልቅ ስትራቴጂካዊ ማስተርፕላን አዘጋጅታለች። ግዙፍ የውሃ ማዞር ፕሮጀክቶች ግብጽ በቶሽካ ፕሮጀክት አማካኝነት ከናስር ሀይቅ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ኩቢክ ሜትር ውሃዎችን ወደ ምዕራብ በረሃ በመቀየር ሰው ሰራሽ ሀይቆች እና ክፍት የመስኖ ቦዮች እንዲፈጠሩ አድርጋለች ። በሌላ በኩል በኒው ዴልታ እና ጂሪያን በሚሊዮን ሄክታር መሬት ለማልማት እና አዳዲስ ከተሞችን ለመገንባት የተፈጥሮ የአባይ ወንዝን አቅጣጫ በመቀየር ቢሊዮን ኩቢክ ሜትር ውሃ በመመደብ ላይ ትገኛለች።እነዚህ ፕሮጀክቶች ግብፅ ለትልልቅ የበረሃ ልማቶች የሚተርፍ ትርፍ ውሃ እንዳላት በተግባር የሚያሳዩ ናቸው። ውሃን መልሶ የመጠቀም አቅም ግብፅ ውሃን መልሶ በማጣራት ጥቅም ላይ ለማዋል ትልልቅ የውሃ ማጣሪያ ጣቢያዎችን ለምሳሌ በህር ኤል ባቃር (Bahr El-Baqar plant) ገንብታለች። ሀገሪቱ በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ኩቢክ ሜትር ፍሳሽ ውሃዎችን መልሳ በመጠቀም ለግብርና በማዋል የምትጠቀመውን እያንዳንዱን የውሃ ጠብታ የማባዛት ከፍተኛ ቴክኖሎጂያዊ አቅም እንዳላት አስመስክራለች። መደምደሚያ አፍሪካውያን የውሃ ሀብታቸውን በጋራ አልምተው ለመጠቀም የሚያደርጉት ጉዞ እውን ሊሆን የሚችለው ግብጽ የምታራምደውን አይነት የተሳሳቱ ትርክቶችን በሳይንሳዊ እውነታዎች መተካት ሲቻል ብቻ ነው። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ይህን በሚገባ ሊገነዘብ ይገባል። ግብፅ ግዙፍ የከርሰ-ምድር ውሃ፣ ዘመናዊ የውሃ ማጣሪያ ጣቢያዎች፣ ከፍተኛ የውሃ መልሶ መጠቀም አቅም እና በበረሃ ውስጥ ውሃ እስከ ማዞር የሚያስችል ሀብት ያላት ሀገር ናት። ይህም ግብፅ የውሃ እጥረት ያለባት ሀገር ሳትሆን፣ የአፍሪካ የውሃ ማማ መሆኗን በተግባር የሚያሳይ ነው።
ኢትዮጵያ፤ አዲሲቷ የዘመን ተሻጋሪ ዲጂታል ክህሎት የተስፋ አድማስ
Aug 7, 2026 265
በሀሪ መልስ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በወፍ በረር “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል። በዛሬው ዕለትም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ አስጀምረናል። ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር፣ እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሠረታዊ ትልሞች ናቸው። እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩም በተለይ የሕዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማትን ማስፋት ላይ ትልቅ ሥራ የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ሥራዎች የመደመር መንግሥት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ ናቸው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ዲጅታላይዜሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የሚመራ ብሔራዊ የልማትና ዕድገት ፕሮግራም ነው። እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2020 በዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ማዕቀፍ ይፋ የተደረገው ብሔራዊ አጀንዳ በዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም ቁልፍ ጉዳይ ሆኖ ተይዟል። ግቡም ሁሉንም ተቋማት በኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ በማስተሳሰር በኢትዮጵያ ፈጣን የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግር መፍጠር ነው። ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት፣ የኢንተርኔትና የዲጅታል ትስስርን ማስፋፋት፣ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎትን ማላቅ፣ ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ የጤና አጠባበቅና የትምህርት ሥርዓትን ማሻሻል፣ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት፣ በኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ እንዲሁም በኢኖቬሽን የሥራ ዕድል መፍጠር እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማትን መደገፍ የዲጅታላይዜሽን መሠረቶች ናቸው። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የዲጅታል ኢኮኖሚ መሠረት ጥሏል። በመንግሥት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥን በዲጅታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል፤ ተጠያቂነት የሰፈነበት የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋትም ብልሹ አሠራርን ለመከላከል የሚያስችል መሠረት ጥሏል። የዲጅታል ማንነትን በማስፋፋት ዜጎች አገልግሎቶችን በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት ማግኘት እንዲችሉ ያስቻለ ሲሆን፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን፣ ቅንጅትንና ተደራሽነትንም አሳድጓል። ቀደም ሲል ዜጎች ዲጅታል ማንነት መጠቀም በማይችሉበት ወቅት በርካታ የወረቀት ሰነዶችን ከማቅረብ ጀምሮ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትን በመዳረስ ረጅም ጊዜና ጉልበት ያጠፉ ነበር። አሁን ግን ሁኔታው ተለውጧል። በወረቀት አልባ ሥርዓት ፈጣንና ፍትሐዊ የመንግሥት አገልግሎት ማግኘት የሚቻልበት የዲጅታል ምህዳር ተፈጥሯል፤ የዜጎች እንግልት ቀንሷል፤ ወረፋና ጥበቃም ተረት ሆኗል። የዲጅታል ክፍያ ሥርዓትም በኢትዮጵያውያን ዘንድ እንደዕለት ተዕለት አጠቃቀም ቀላልና የተለመደ እየሆነ መጥቷል። የቴሌኮም መሠረተ ልማትን የማስፋፋት ሥራም ተጠናክሯል፤ የዲጅታል ክህሎት በተለይም በወጣቶች ዘንድ አዲስ የእውቀትና የተወዳዳሪነት መሣሪያ ሆኗል። ለዲጅታል መሠረተ ልማት መስፋፋት ቁልፍ የሆኑ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፎችም ተፈጥረዋል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግር መሠረት ጥሏል፤ የኢትዮጵያን መጪ ጊዜ በተስፋ መመልከት የሚያስችል አጉሊ መነጽር አቅርቧል። በዲጅታል ክፍያዎች የታገዘ የጥሬ ገንዘብ አልባ ግብይትም የሀገሪቱን አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እያዘመነ ይገኛል። ጥሬ ገንዘብ በእጅ የመያዝ ልማድ መቀነሱ የገንዘብ ማተሚያና ማጓጓዣ ወጪን ቀንሷል፤ የገንዘብ ዝውውርን ግልጽና ፈጣን በማድረግም ሕገወጥ አሠራሮችንና ሙስናን ለመከላከል አስችሏል። ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ጥበቃ ከተደረገለት የፋይናንስ ሥርዓት ጋር ሲቀናጅም፣ ሕዝቡ በዲጅታል ክፍያዎች ላይ ያለው መተማመን እንዲጎለብት ያደርጋል፤ የሀገሪቱንም የዲጅታል ሽግግር ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል። ይህም ለዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሠረት ጥሏል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030፤ የሽግግሩ ቀጣይ ምዕራፍ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የመንግሥትና የግል ዘርፍ አጋርነትን በማጠናከር፣ የኤሌክትሮኒክ የመንግሥት አገልግሎቶችን ፍጥነት፣ ተደራሽነትና ግልጽነት ለማሳደግ ያለመ ነው። ይህም የመንግሥትን ወጪ ለመቀነስና የአገልግሎት ብቃትን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬትም በኢኮኖሚ፣ በትምህርትና በአገልግሎት ዘርፎች አዎንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። የሀገሪቱ የዲጅታል ሽግግር በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ላይ በተመሠረተው የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ላይ የተቃኘ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስትራቴጂ ማስጀመሪያው ወቅት፦ ስትራቴጂው በከተማም ሆነ በገጠር የዲጅታል ሥርዓትን በማስረጽ የዲጅታል ኢኮኖሚን እውን የምናደርግበት ነው ብለዋል። ቁሳዊ ዕድገት የሚጀምረው የሰው ኃይል አቅምን በመገንባት እንደሆነ ጠቅሰው፣ ወጣቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ፣ የፈጠራ ባለቤቶችና ሥራ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ በዲጅታል ክህሎት ማስታጠቅ እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥተዋል። የዲጅታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂያዊ ግቦች ኢትዮጵያ የብሮድባንድና ኢንተርኔት ተደራሽነትን በመላ ሀገሪቱ በመዘርጋት፣ የዜጎችና ተቋማትን የዲጅታል ክህሎት በማሳደግ፣ እንደ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ስታርትአፖችን በቴክኖሎጂ በማዘመን የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትና ንግድን መሳብ፣ እንዲሁም አካታች የዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት ናቸው። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የመንግሥት የዲጅታል አገልግሎት ማስፋፊያ፣ የቴሌኮም ሪፎርም፣ ዲጅታል ክፍያ፣ ብሔራዊ የዲጅታል መታወቂያ/ፋይዳ፣ እንዲሁም በሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ ዲጅታል የሕዝብ መሠረተ ልማት፣ የሳይበር ደህንነትና ብሔራዊ የዲጅታል አካታችነትን መርህ ያደረገውን የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አዋልዷል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጅታል ሽግግር ስትራቴጂ ነው። ከዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬት የተቀዳ ታላቅ የመሆን ህልም ሥጋ ለብሶ የታየበት ግልጽ ፍኖተ ካርታም ነው። የዲጅታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፣ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2030 ቀልጣፋ የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ፣ የአስተዳደር ሥርዓትን በማጠናከር አገልግሎትን ማሻሻል፣ በዲጅታል ቴክኖሎጂ የበቃ ማኅበረሰብ በመፍጠር ሀገርን ማበልጸግ፣ ለነገ ዛሬ የሚኖር አደራና ዛሬ የነገ ስንቅ ሆኖ በግልጽ ሰፍሯል። የኢትዮጵያ የዲጅታል ሽግግር ግብ አንድ ነው፤ አካታችና ዘላቂ ዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት፣ በዋጋ ተመጣጣኝና ተደራሽ የኢንተርኔትና የኮሙኒኬሽን አገልግሎትን ማስፋት፣ በዲጅታል ኢኮኖሚ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የመረጃ አስተዳደርና የሳይበር ደህንነት ጥበቃን ሕልው ማድረግ፣ የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን መጨመር፣ ዲጅታል ክህሎትና ኢኖቬሽንን ማሳለጥ ነው። ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/፤ የዲጅታል ሽግግር መልህቅ ''በቅርብ ዓመታት ውስጥ፣ ዲጅታል ማንነት ተስፋ ሰጪ ከሆነው ፈጠራ ወደ ዲጅታል ሽግግር መሠረታዊ ምሰሶ ተሻሽሏል። ከአሁን በኋላ አማራጭ ሳይሆን፣ ሰዎችን ከአገልግሎቶች፣ ከማኅበረሰቦች፣ ከተቋማት እና ከመንግሥታት ጋር የሚያገናኝ አስፈላጊ መሠረተ ልማት ነው። ፋይዳ ካርድ ብቻ አይደለም። የግለሰቦችን የግል መረጃ ምሥጢራዊነት በመጠበቅና አስፈላጊ የሆነውን መረጃ ብቻ በማጋራት ማንነትን የሚያረጋግጥ ልዩ መለያ ቁጥር ነው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/፤ የዲጅታል ሽግግር መልህቅ የዲጅታል ብሔራዊ መታወቂያ /ፋይዳ/ (National Digital ID) በኢትዮጵያ ሥራ የጀመረው እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2023 ነበር። ምንም እንኳን የፕሮጀክቱ ዝግጅትና ሕጋዊ መሠረት ቀደም ብሎ የተጀመረ ቢሆንም፣ በአዋጅ ቁጥር 1284/2015 በሕግ ተቋቁሟል። እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር ከ2019 እስከ 2020 ባለው ጊዜም ፋይዳ በዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ አካል ሆነ። ከዚያም ምዝገባው በመላ ኢትዮጵያ ተስፋፍቶ፣ ከመንግሥት አገልግሎቶች፣ ከባንኮች፣ ከዲጅታል ክፍያ ሥርዓት እና ከመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት ጋር ተሳስሯል። በኢትዮጵያ እያንዳንዱን ነዋሪ የአንድ ልዩ የዲጅታል መለያ ባለቤት ማድረግ የፕሮጀክቱ ዋነኛ ግብ ነው። ይህም የመንግሥትና የግል አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበትን ሥርዓት ለመዘርጋት፣ የማንነት ማጭበርበርና ድርብ ምዝገባን ለማስቀረት እንዲሁም የኢትዮጵያን ዲጅታል ኢኮኖሚ ለመደገፍ ያስችላል። ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የነዋሪዎችን የባዮሜትሪክና ዲሞግራፊክ መረጃ በመሰብሰብ፣ ''አንድ ሰው፣ አንድ ማንነት” በሚል መርህ እያንዳንዱን ሰው ልዩ በሆነ ሁኔታ መለየት የሚያስችል ሥርዓት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ስለፋይዳ አስፈላጊነት ሲናገሩ፣ “ፋይዳ በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣ በትግርኛ፣ በሱማሊኛ፣ በአፋርኛ እንዲሁም በአረብኛ፣ በሂንዱኛና በተርኪሽ ቋንቋዎች ፋይዳ ነው። … ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/ በጣም ጠቃሚ ነገር ነው፤ ከሕዳሴ የሚያንስ አይደለም። እንደ ሀገር ዲጅታል መታወቂያ ብንሠራ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርት በሰባት ፐርሰንት ይጨምራል። ፋይዳ የመተማመኛ ሥርዓት ነው…” በማለት የፋይዳን መልከ ብዙ ፋይዳ ገልጸዋል። ፋይዳ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግሩን ለማሳለጥ ቁልፍ መሣሪያ መሆኑንም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ከ150 በላይ ተቋማት ጋር ተሳስሯል። ከ48 ሚሊዮን በላይ ዜጎችም ተመዝግበዋል። እስከ 2020 ዓ.ም ድረስ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ወደ 115 ሚሊዮን ለማድረስ ጉዞው ቀጥሏል። በዚህም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ወደ መደበኛ የፋይናንስ ሥርዓት ለማስገባት እያገዘ ይገኛል። መንገዶች ሁሉ ኢትዮጵያን ወደ ዲጅታል ሽግግር በሚወስዱበት ሀዲድ፣ ፋይዳ መሪ ተዋናይ ሆኖ ይቀጥላል። ዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት እንዲያገኙ፣ የባንክና የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲጠቀሙ የሚያስችል የቴክኖሎጂ ምህዳር ይፈጥራል። መንግሥትም ማጭበርበርን ለመከላከል፣ በተቋማት መካከል ግልጽና የተቀናጀ ትብብርን ለመዘርጋት እና የተሻለ የሕዝብ አገልግሎት የሚሰጥበትን ዕድል እውን ለማድረግ ፋይዳን ይጠቀማል። የቢዝነስ አንቀሳቃሾችም ዲጅታል ግብይትን፣ ፋይናንስንና ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሥራቸውን የበለጠ ቀልጣፋና ተደራሽ ማድረግ ይችላሉ። በአጭሩ፣ ፋይዳ ''ሁሉ በእጄ፣ ሁሉ በደጄ” የሚለውን የዲጅታል ኢኮኖሚ ራዕይ እውን ለማድረግ የሚያግዝ ቁልፍ መሠረተ ልማት ነው። መሶብ፤ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት የጊዜና የቦታ ልጓም ''ሀገራዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሠረታዊ የሆነ የባህል ለውጥ ያስፈልጋል። ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን እንገኛለን። መሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትን ተግባራዊ ማድረግ የጀመርነው በቅርብ ጊዜ ቢሆንም፣ በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል። ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያመላክታል።”ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት፤ የጊዜና የቦታ ልጓም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 12 የፌዴራል ተቋማት 40 የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር እንዲሰጡ በማድረግ ሚያዚያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ሥራ ጀምሯል። እነሆ ማዕከሉ የተቋማትንና የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ቁጥር እያሳደገ የኢትዮጵያን የዲጅታል ሽግግር ፍኖት እየቀረጸ ይገኛል። ዜጎችም በዲጅታል መሠረተ ልማት የተደገፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። ከዚህ በፊት የዜጎችን ጊዜ የሚያባክኑ ረጅም ወረፋዎች፣ የተለያዩ ቢሮዎችን ደጋግሞ መጎብኘት፣ “ሰነድ ይጎድላል፣ ኮፒ አድርገህ አምጣ” የሚሉ የወረቀት ሥራዎች በአዲሱ የአገልግሎት ሥርዓት እየተቀየሩ ነው። አዲስ የአገልግሎት አድማስ የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ220 በላይ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ሕንፃ ሥር በማቅረብ የዜጎችን የጊዜና የቦታ ጫና ቀንሷል። ከቀበሌ መታወቂያ ማውጣት ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የንግድና የጉምሩክ አገልግሎቶች ድረስ በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበት ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል። ፈጣንነት፣ ቅልጥፍና፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና መርሆዎች ሆነዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ባስጀመሩበት ወቅት፤ ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፣ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ብለዋል። የዲጅታል አገልግሎት የዜጎችን ጊዜና ጉልበት የሚቆጥብ አዲስ የአስተዳደር ባህል መሆኑን ገልጸዋል። በአጠቃላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የወረቀት እና የወረፋ ዘመንን በመቀየር ዜጋን ማዕከል ያደረገ፣ ቀልጣፋና ዲጅታል የሆነ የአገልግሎት ሥርዓት እየገነባ ያለ የለውጥ ምሳሌ ሆኗል። የ5-ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ፤ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያ መድረክ በዲጅታል ዘመን የሰው ኃይል አቅም የሀገራት የዕድገት መሰረት እሆነ ነው። ኢትዮጵያም የወጣቶቿን የፈጠራና የቴክኖሎጂ አቅም ለማሳደግ ትልቅ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያ መርሃ ግብር ጀምራለች። የ5-ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ የወጣቱን ትውልድ የፕሮግራሚንግ፣ የሶፍትዌር ልማት፣ የፈጠራ ሥራና የዲጅታል ቴክኖሎጂ አቅም ለማጎልበት የተቀረፀ ሀገራዊ አጀንዳ ነው። መርሃ ግብሩ ወጣቶችን የዲጅታል ኢኮኖሚ ተሳታፊዎች ብቻ ሳይሆኑ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎችና የሀገር በቀል መፍትሔ አበልጻጊዎች ለማድረግ ያለመ ነው። ''ይህም ኢትዮጵያ በዓለም የዲጅታል ውድድር ውስጥ የምትኖራትን ሚና ለማሳደግ፣ የቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና በአፍሪካ የፈጠራ ማዕከል ለመሆን የሚያግዝ የወደፊት ራዕይ ነው። ኢትዮጵያ ወደፊት የሚያልሙ አሳቢ ወጣት ዜጎቿ ተስፋ አላት። የ‘አምስት ሚሊዮን ኮደርስ’ መርሃ ግብር ታላቅ እድል ነው። አምስት ሚሊዮኖቹ ኮደሮች ሀገር በቀል መፍትሔዎችን የሚሰጡ ብቻ ሳይሆኑ፣ ለአህጉራችን የተስፋ ብርሃን የሚፈነጥቁ ናቸው።''ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአጠቃላይ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ የዲጅታል ክህሎትን ከመገንባት ባሻገር፣ የወጣቱን የፈጠራ ኃይል ወደ ሀገራዊ የዕድገት ሞተር ለመቀየር የተቀረፀ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ዋነኛ መሠረት ነው። 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ፤ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያና የወጣቱ የወደፊት አቅም በፍጥነት በሚለዋወጠው የዲጅታል ዓለም ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት መያዝ አማራጭ ሳይሆን የዘመኑ ግዴታ ሆኗል። ዛሬ ላይ በመትጋት ነገን ማልማት የእያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ሲሆን፣ የሀገር ዕድገትም የሰው ኃይል አቅም ግንባታ ላይ ይመሰረታል። መንግሥት የበለጸገችና በቴክኖሎጂ የተደገፈች ኢትዮጵያን ለመገንባት ከለያቸው አምስት ቁልፍ የትኩረት መስኮች መካከል አይ.ሲ.ቲ (ICT) አንዱ ነው። በዚህ ራዕይ መሠረት የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማሳለጥ ሦስት ቁልፍ የዲጅታል ሽግግር ማስፈጸሚያዎች ተግባራዊ ሆነዋል። እነሱም መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት፣ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ ናቸው። የወጣቱን የዲጅታል አቅም የሚገነባ ታላቅ ኢንሼቲቭ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ትብብር ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ በሦስት ዓመታት ውስጥ 5 ሚሊዮን ወጣቶችን በዲጅታል ክህሎት ለማሰልጠን የተቀረጸ ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሚንግ (Programming)፣ የመረጃ ትንተና (Data Analysis)፣ የአንድሮይድ ልማት (Android Development) እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት መሠረቶች (Artificial Intelligence Fundamentals) የሥልጠናው ዋና የክህሎት ዘርፎች ናቸው። ኢንሼቲቩ የተያዘለትን ግብ በፍጥነት እያሳካ ይገኛል። ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበዋል፤ ቁጥሩን እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም 7 ሚሊዮን ለማድረስ ዕቅድ ተይዟል። ይህም የወጣቶችን ለሥራ ዓለም ተፈላጊነት ከማሳደግ ባሻገር፣ የሀገሪቱን የዲጅታል የሰው ኃይል ልማት ያጠናክራል። በመንግሥት ተቋማት የሶፍትዌር ልማትና የዲጅታል ሽግግር ሥራዎችን የሚያሳልጡ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችንም ያፈራል። በኢንሼቲቩ አማካኝነት 1 ሚሊዮን የዲጅታል የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ከዲጅታል ምርቶች ወጪ ንግድ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት የተቀመጠው ዕቅድ የፕሮግራሙን ሀገራዊ ፋይዳ ያመላክታል። የወጣቶች የፈጠራ ኃይል የኢትዮጵያ የዲጅታል ተስፋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየትኛውም የትምህርትና የዕውቀት ደረጃ ላይ ያሉ ወጣቶች የአምስት ሚሊዮን ኮደሮች ፕሮጀክትን በመጠቀም ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ ጥሪ አቅርበዋል። የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከላት፣ አሰልጣኞችና ዩኒቨርሲቲዎችም የፕሮግራሙን ስኬት ለማስፋት የሚያደርጉት አስተዋፅኦ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጅታል ሽግግር ሦስቱ ምሰሶዎች በጥቅሉ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ፣ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የኢትዮጵያን የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያስፈጽሙ ተያያዥ ምሰሶዎች ናቸው። ኮደርስ የዲጅታል ኢኮኖሚውን የሚገነባና የሚያስፋፋ የሰው ኃይል ያበረክታሉ፤ ፋይዳ ደግሞ የደህንነቱ የተጠበቀ የዲጅታል ማንነት ሥርዓት ይፈጥራል፤ መሶብም በአንድ ጣሪያ ሥር ፈጣንና ግልጽ የህዝብ አገልግሎት ያሳልጣል። ከዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ራዕይ ጋር ተጣምረው እነዚህ ሦስት የለውጥ ምሰሶዎች ኢትዮጵያን ወደ አካታች፣ ዘላቂና ተወዳዳሪ የዲጅታል ኢኮኖሚ ለማሸጋገር የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው። ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የኢትዮጵያ ተሻጋሪ ህልሞች መመልከቻ በኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እ.ኤ.አ. በ2020 የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመመስረት ተቋማዊ መሠረት የያዘ የልማት አቅጣጫ ሆኗል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፖሊሲና ሕጋዊ ማዕቀፎች በመዘርጋታቸው ዘርፉ በተደራጀ አሠራር እንዲመራ ተደርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጎበኙበት ወቅት፣ ሰው የጠራ ራዕይ ካለው፣ በከፍተኛ ዲሲፕሊን የሚሠራ ከሆነ ያሰበውን ማሳካት እንደሚችል፤ ኢትዮጵያ ብቃት ያላት ሀገር መሆኗን በመግለጽ የዘርፉን ሀገራዊ ጠቀሜታ አስረድተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሀገር ውስጥ የፈጠራ አቅምን በማበረታታት ዘርፈ ብዙ ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች እንዲመነጩ እያደረገ ይገኛል። በግብርና፣ በጤና፣ በፋይናንስ፣ በደህንነትና በአገልግሎት ዘርፎች የሚያገለግሉ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መፍትሔዎች በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች መፍጠር ጀምረዋል። በአማርኛ፣ ኦሮምኛና ትግርኛ ቋንቋዎች የተዘጋጁ የጽሑፍና የድምፅ ማቀናበሪያ ቴክኖሎጂዎች (NLP)፣ በጤና ዘርፍ የጡት ካንሰር፣ የስኳር በሽታና የሳንባ በሽታዎችን በምስል ምርመራ ቀድመው ለመለየት የሚያግዙ የAI መፍትሔዎች፣ በግብርና ዘርፍ የቡናና የሰብል በሽታዎችን የሚለዩ መተግበሪያዎች እየተስፋፉ ነው። በተጨማሪም ለከተማ ደህንነት፣ ለፖሊስ ሥራ፣ ለጉምሩክ ቁጥጥርና ለፋይናንስ ተቋማት የሚያገለግሉ ቻትቦቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች በመስኩ እየተተገበሩ ይገኛሉ። የታዳጊዎች የሰመር ካምፕ የAI ስልጠናዎችም የወደፊቱን የቴክኖሎጂ ባለሙያ ትውልድ ለማፍራት እያገዙ ናቸው። የኢትዮጵያ የዲጅታል ሽግግርና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ጉዞ በሀገር ድንበር የማይገደብ፣ የአፍሪካን ዲጂታል ሽግግር ታሳቢ ያደረገ አህጉራዊ ራዕይ ነው። ለዚህም ኢትዮጵያ የፓን አፍሪካ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኮንፈረንስን በማዘጋጀት አፍሪካ በዲጂታል ሽግግር፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ ትብብር እንድትጠናከር ያላትን ራዕይ አሳይታለች። በአፍሪካ ቀዳሚ ከሚሆኑ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከላት አንዱ የሆነው የAI ዩኒቨርሲቲ ግንባታም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ለማሳካት፣ የአፍሪካን የቴክኖሎጂና የፈጠራ አቅም ለማሳደግ የተያዘ ተሻጋሪ ራዕይ ነው። በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ለኢትዮጵያ የወደፊት የዕውቀት ኢኮኖሚ፣ የፈጠራ አቅምና የዲጂታል ሉዓላዊነት መሠረት እየሆነ የሚሄድ ተሻጋሪ መሣሪያ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር፤ የዲጅታል ሉዓላዊነት እና ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ዘብ የዓለም የዲጅታላይዜሽን ሽግግር በብርሃን ፍጥነት እየተስፋፋ ባለበት ዘመን፣ ቴክኖሎጂን መጠቀም ብቻ ሳይሆን የዲጅታል መሠረተ ልማቶችን ከሳይበር ስጋቶች መጠበቅ የሀገራት ቁልፍ ተግባር ሆኗል። በዚህ የቴክኖሎጂ ውድድር ዓለም የመረጃ ደህንነት ከቴክኒክ ጉዳይ ባለፈ የሀገር ሉዓላዊነትና ህልውና ጉዳይ እየሆነ መጥቷል። ኢትዮጵያም የዘግይቶ መግባት ጥቅም (Latecomer Advantage) በመጠቀም የዲጅታል ሽግግሯን በዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ላይ ለመገንባት እየሠራች ትገኛለች። ይህንን የዲጅታል ጉዞ አስተማማኝ ለማድረግና የሀገሪቱን የመረጃ ሀብት ለመጠበቅ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ወሳኝ ሚና እየተወጣ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የኢትዮጵያን የኢንፎርሜሽን ሥርዓቶችና ቁልፍ የመረጃ መሠረተ ልማቶች ከሳይበር ጥቃት የመጠበቅ፣ የመረጃ ደህንነትን የማረጋገጥና ብሔራዊ ጥቅሞችን የማስከበር ተልዕኮ ተሰጥቶታል። የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ፣ የደህንነት ኦፕሬሽን ማዕከላት (Security Operation Centers) እና የዲጅታል ፎረንሲክ ላቦራቶሪዎች ግንባታ ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። እነዚህ ዘመናዊ የዲጅታል ደህንነት መሠረተ ልማቶች እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም፣ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ቁልፍ ሀገራዊ ተቋማትን ከተወሳሰቡ የሳይበር ጥቃቶች አስቀድሞ ለመከላከል፣ አደጋ ቢከሰትም ፈጣን ሕጋዊና ቴክኒካዊ ምላሽ ለመስጠት ያስችላሉ። የመረጃ ደህንነት፤ የዲጅታል ኢኮኖሚ መሠረት በዛሬው ዓለም መረጃ (Data) እንደ አንዱ ዋና ሀብት በመቆጠሩ፣ የዜጎችን ግላዊ መረጃ፣ የፋይናንስ ግብይቶችንና የመንግሥት ሚስጥራዊ መረጃዎችን በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ የዲጅታል ሉዓላዊነት ዋና መሠረት ሆኗል። ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ሥርዓት መኖሩ ዜጎች በዲጅታል አገልግሎቶች ላይ እምነት እንዲያሳድሩ፣ የግልና የውጭ ባለሀብቶችም በኢትዮጵያ የዲጅታል ኢኮኖሚ ላይ የተሻለ እምነት እንዲኖራቸው ያደርጋል። በዚህም የሳይበር ደህንነት የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ስኬትን የሚደግፍ ዋና የጥበቃ መሠረት ሆኖ ይቀጥላል። ማጠቃለያ፡ ዲጂታል ኢትዮጵያ፤ የወደፊት ተወዳዳሪነት መሠረት የኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር ጉዞ ከፖሊሲ ቀረጻ እስከ ተግባራዊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ዝርጋታ በፍጥነት እየተሻገረ ይገኛል። ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሚመራ ሲሆን፣ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ /ፋይዳ፣ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት፣ አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ልማትና የሳይበር ደህንነት ሥርዓት ዋና ዋና የሽግግሩ ምሰሶዎች ሆነዋል። ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ /ፋይዳ የዜጎችን ዲጂታል ማንነት በማረጋገጥ ለዲጂታል አገልግሎቶች መሠረት ሲሆን፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሕዝብ አገልግሎትን በፍጥነት፣ በቅልጥፍናና በግልጽነት ለማቅረብ አዲስ የአሠራር ባህል እየገነባ ነው። አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ደግሞ ለዲጂታል ኢኮኖሚው የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል በማፍራት የቴክኖሎጂ ፈጠራና የዲጂታል ሥራ ዕድል እድገትን ያፋጥናል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዩኒቨርሲቲና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ልማት ተቋማት የወደፊቱን የእውቀትና የፈጠራ አቅም ለመገንባት ወሳኝ ሚና ይኖራቸዋል። በተመሳሳይም የሳይበር ደህንነት ሥርዓት የዲጂታል ኢኮኖሚውን ከስጋቶች የሚጠብቅ፣ የመረጃ ደህንነትንና የሀገር ዲጂታል ሉዓላዊነትን የሚያስከብር ጠንካራ ጋሻ ሆኖ ይቀጥላል። በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽንና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፎች ኢትዮጵያ እየወሰደች ያለችው መዋቅራዊ እርምጃ የአገር ውስጥ አገልግሎቶችን ከማዘመንና የዜጎችን ኑሮ ከማቅለል ባለፈ፣ ሀገሪቱን በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ፣ አካታችና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ኢኮኖሚ ባለቤት ለማድረግ የሚያግዝ ነው። ኢትዮጵያ አዲስ የተስፋ አድማስ፡- '’ኢትዮጵያዊነት ያስተማረን ትልቁ እውነት፤ በጊዜያዊ ፈተናዎች ተሸንፎ መውደቅ ሳይሆን፣ ችግሮችን ወደ ዕድል፣ ፈተናዎችንም ወደ ስኬት መለወጥና ድልን መቀዳጀት ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ያስመዘገባቸው ውጤቶች ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ቀጣይ የልህቀት ጉዞ ጠንካራ መነሻና መሠረት ይሆናሉ። በመሆኑም ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታዋን ለማፋጠን በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተጀመሩ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተቀናጀ መንገድ በጋራ ገቢራዊ ማድረግ ይጠበቅባታል። ዲጂታል ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የእውቀት፣ የፈጠራና የተወዳዳሪነት ሀገራዊ መሠረት ነው።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 11654
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 21489
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14515
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20266
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
በምክክር እንጂ በመሳሪያ ድምጽ ሀገር አይገነባም
Aug 8, 2026 349
ኢትዮጵያ የዛሬ ማንነቷና ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እዚህ እንድትደርስ በርካታ ውጣውረዶችን አልፋለች። በቀደመ ታሪኳም ዜጎች በራሳቸው የውስጥ ጉዳይ መስማማት ባለመቻል እርስ በእርስ ካደረጓቸው ግጭቶች ባለፈ የውጭ ሃይሎችም የራሳቸውን አሉታዊ ጫና ሲፈጥሩ ቆይተዋል፤ አሁንም ይህንኑ ለማስቀጠል ተላላኪዎቻቸውን ለመጠቀም ሲሞክሩ ይታያል። በአንድ ሃገር ውስጥ የማያግባቡ ጉዳዮች በየትኛውም አጋጣሚና የታሪክ ምዕራፍ ሊያጋጥሙ ይችላሉ። እነዚህን ችግሮች በሃይል ለመፍታት የሚደረገው የመሳሪያ ትንቅንቅ ግን አክሳሪና ዘመን እያለፈበትም ነው። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ሰላማዊ የእድገት ጉዞ ለማወክ የህዝቦቿን አንድነት ለመበጥበጥ ከቅርብም ሆነ ከሩቅ የሚመጡ ጠላቶች ጠፍተው አያውቁም። በየዘመናቱ የተሻገርናቸው የታሪክ ስብራቶችን ፣ የመብት ጥያቄዎችንና ሌሎችንም መነሻ በማድረግ በውስጥ ባንዳዎች እና በውጭ ባዳዎች አማካኝነት የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ለመክተት፣ የብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚደረጉ ሴራዎች ዛሬም ላይ ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት ተሰሚነትና ተጽዕኖ የሚያሳምማቸው ለዜጎቿን እኩል ተጠቃሚነትና ብልጽግና መረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚያስጨንቃቸው እነዚህ ሃይሎች በመብት ፣ በነጻነት፣ በዴሞክራሲ፣ በማንነትና በሌሎችም የሃሰት ትርክቶች መነሻነት በሩቅ ቢያቅታቸው በቅርብ የውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን እያደራጁ በጀት መድበው የጦር መሳሪያ አቅርበው ሀገር የማፍረስ ሙከራቸውን አላቋረጡም። በመደመር እሳቤ ሁሉንም በአንድ ላይ በማቀራረብና የጋራ ትርክቶችን በመገንባት ከልዩነት ይልቅ የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ዘላቂ ልማቷን መፃኢ ብሩህ ተስፋዋን ለማለምለም በሁሉም ዘርፍ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ተሳትፎ እየሰራች መሆኗም ምቾት ነስቷቸዋል። በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሔደ ያለውና ወርቃማው እድል ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ፣ የሚያስችሉ ወሳኝ ምዕራፎች ላይ ደርሷል ። በዚህ የምክክር ሒደት በሀገሪቱ የትኛውም ጥግ ያለ ዜጋ እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የተወከሉበት ፣ የብሔር፣ የፖለቲካ አመለካከትና የሃይማኖት ልዩነት የማያደናቅፉት ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እየተካሔደ ይገኛል። ጥያቄያችንን በጠብመንጃ አፈሙዝ እንፈታለን ያሉ ታጣቂዎችም ብረት በማስቀመጥ አጀንዳዎቻቸውን ይዘው ወደ ጠረጴዛው ቀርበዋል። ልክ ናቸው ሀገር ከሁሉም ነገር ትበልጣለችና ይሄንን ወርቃማ እድል ለመጠቀም ማሰብ ትክክለኛው ውሳኔ ነው። በትጥቅ ትግል ጥያቄያችንን እንመልሳለን በሚል ሽፋን የሌሎችን አጀንዳ ለማሳካት የሚደረግ ጥረት የሃገርና የትውልድ ጠባሳ ከማስቀመጥና የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው መገንዘብ ብልህነት ነው። የዚህ ምክክር ተሳታፊ/ተመካካሪ ከሆኑት የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) አመራር ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በዚህ ይስማማሉ ። ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ተስፋ የጣልንበት፣ በንግግር፣ በምክክር ሀገራችንን የምናስቀጥልበት፣ ሁሉም ተነጋግሮ ተመካክሮ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ከችግሮች ነፃ የሚያደርግበት ነው ይላሉ። ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚነጋገርበት፣ የሚመካከርበት እና በሃሳብ የበላይነት ጠንካራ ሃገር የሚፈጠርበት መልካም የታሪክ አጋጣሚ መሆኑንም ይናገራሉ። በምክክር፣ በድርድር የሕዝብን ጥያቄ በመመለስ ሀገርን የምናስቀጥልበትና የውጭ ኃይሎችን ጣልቃ ገብነት የምናስወግድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ነው ብለዋል። የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራር የቀድሞ ታጣቂ ጃል ሰኚም ይሄንኑ ሃሳብ ይጋራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ለዓመታት የቆዩ ልዩነቶችን ለመፍታት ሀገራዊ ምክክር መዘጋጀቱ ትልቅ እርምጃ እንደመሆኑ እሳቸውም ያላቸውን ሀሳብ በማንጸባረቅ እየመከሩ ይገኛሉ። እርሳቸውና ቡድናቸው ከዚህ ቀደም የትጥቅ ትግልን በመምረጥ ጫካ ገብተው እንደነበር አስታውሰው፤ ችግሮችን በመሳሪያ ከመፍታት ይልቅ በሰላማዊ የምክክር መድረክ መፍታት ጥሩ አማራጭ መሆኑን አምነው ወደ ሰላም መንገድ መምጣታቸውንም ተናግረዋል። ችግሮቻቸውን በምክክር የፈቱ ሀገራት በሁሉም ዘርፍ ዕድገታቸውን የሚያስቀጥሉ ሲሆኑ ወደ ትጥቅ ትግል ያመሩና ግጭት ውስጥ የገቡት ደግሞ በፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውድቀት ለከፋ ድህነት መዳረጋቸውን ጠቅሰዋል። የጦር መሣሪያ በመነቅነቅና ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ በመግባት የሚፈታ ችግር እንደሌለ የሚናገሩት ደግሞ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ(አብን) አመራሩ ተመካካሪ ጣሒር መሀመድ ናቸው። ጫካ ባለውና እዚህ ባለው ሰው መካከል ምንም ዐይነት የዜግነት ልዩነት እንደሌለ ገልጸው ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሃሳብ ለመታገል ልዩነቱን ለማቅረብ የፈለገ ሁሉም ዜጋ በምክክሩ የመሳተፍ ነጻነት እንዳለው ገልጸዋል። በሃገራዊ ምክክሩ ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሰላማዊ መድረክ መወያየት የተመረጠበት ዋና ምክንያት ዘላቂ ሰላም፣ አገራዊ መግባባት እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ ለማምጣት ነው:: የትጥቅ ትግል የዜጎችን ህይወት ያጠፋል፣ መሰረተ ልማቶችን ያወድማል፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድቀትንም ያመጣል: ፤ ሰላማዊ መድረክ ግን ያለምንም ደም መፋሰስ ሃሳብን በሃሳብ ለመሞገት እድል ይሰጣል:: በኃይል የሚመጣ ለውጥ ብዙውን ጊዜ አሸናፊና ተሸናፊን ስለሚፈጥር የቁስል እና የቂም ዑደትን ያስቀጥላል:: በሰላማዊ ውይይት የሚገኝ መፍትሄ ግን የሁሉንም ወገን ስጋት እና ፍላጎት ያገናዘበ በመሆኑ ዘላቂነት ይኖረዋል:: ሃገራዊ ምክክሩ የታጠቁ አካላትም ጭምር መሳሪያቸውን አስቀምጠው በሃሳብ እንዲፎካከሩ መንገድ ከፍቷል። ይህ ታሪካዊና ወርቃማ እድል ኢትዮጵያዊንን አግባብቶ ወደተረጋጋችና የበለጸገች ሃገር የሚመራ በመሆኑ ስኬታማነቱ አያጠራጥርም። ለእድለኛው ትውልድ ያጋጠመው ወርቃማው ስጦታ ሃገራዊ ምክክር የተቋቋመለትን ዓላማ ያሳካል።
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 1240
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።