ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፍሪካ ሕብረት የጤና ዘርፍ ጉባኤ ለመሳተፍ ጋና ገቡ
Jul 21, 2026 9
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፦የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፍሪካ ሕብረት የጤና ዘርፍ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ጋና ገብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሙኤል ኦኩዜቶ አብላክዋ እና ሌሎች የሀገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።   የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ልዩ ጉባኤ በጤና ዘርፍ ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚካሄድ ሲሆን፤ በዋናነትም እ.ኤ.አ. በ2030 በአህጉሪቱ ኤች አይ ቪ ኤድስን ከሕብረተሰብ ጤና ስጋትነቱ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ፣ የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞትን መግታት፣ በአህጉሪቱ ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር፣ እንዲሁም የጤና ስርዓቶችን በስትራቴጂካዊ ባለቤትነትና በራስ አቅም ለማጠናከር የሚያስችል ዘላቂ የፋይናንስ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት ላይ ይመክራል።   በጉባኤው የኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ ስኬታማ ተግባራትን ተሞክሮ ለአህጉሪቱ መሪዎች ታካፍላለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጋና በሚኖራቸው ቆይታ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ግንኙነትን ይበልጥ በሚያጠናክሩና ቀጣናዊ ትብብርን በሚያሳድጉ ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመመከት ረገድ የማይተካ ሚናዋን እየተወጣች ነው-አምባሳደር ሃደራ አበራ
Jul 21, 2026 32
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመከላከል ረገድ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት 1354ኛ የሚኒስትሮች ስብሰባውን ዛሬ በበይነ መረብ አካሂዷል።   ስብሰባው በአፍሪካ ሽብርተኝነትና በዓመፅ የታጀበ ጽንፈኝነትን መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል። አምባሳደር ሃደራ አበራ ዓለም አቀፍ የሽብርተኛ ቡድኖች በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት የደቀኑትን ስጋት አንስተዋል። የሽብርተኛ ቡድኖች ዲጂታል አማራጮች እና ማህበራዊ ሚዲያ ጨምሮ ቴክኖሎጂዎችን አባላትን ለመመልመል፣ ፕሮፓጋንዳ ለማሰራጨት እና ጽንፈኝነትን ለማስፋፋት እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ አመልክተዋል።   ዓለም ላይ ያሉ ለውጦችን ከግምት ውስጥ በማስገባት የአፍሪካ ተጠባባቂ ኃይልን ወደ ስራ ማስገባት እና የአፍሪካ ሀገራት በደህንነት እና አስተዳደር ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ አህጉራዊ የአሰራር ማዕቀፎችን በሚገባ መተግበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። አምባሳደር ሃደራ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ሽብርተኝነትን ለመከላከል እና በቀጣናው ያለውን የሽብርተኝነት ነቀርሳ ለማስወገድ እያደረገች ያለውን የማይተካከል አስተዋጽኦ ማንሳታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!
Jul 21, 2026 90
የሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ዐበይት መረጃዎች በትናንትናው ዕለት በቡድን ተከፋፍለው መመካከር የጀመሩት ተመካካሪዎች ዛሬም በየቡድናቸው በመሆን መመካከር ቀጥለዋል፡፡ 50 ተመካካሪዎችን በመያዝ በ80 ቡድን ተከፋፍለው መመካከር የጀመሩት ንዑሳን ቡድኖች በተሟላ ሁኔታ ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ በየንዑስ ቡድናቸው አስር አስር በመሆን ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ሂደት እስከ ነገ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በዚህ ሂደት ተመካካሪዎች በሚመካከሩባቸው የአጀንዳ ሃሳቦች ላይ በርካታ ሃሳቦችን እና ምልከታዎችን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡ሂደቱ ተመካካሪዎች ላለመግባባት መንስኤ የሆኑ እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ አመለካከቶችን እና ምክንያቶችን ከስር መሰረቱ አንዳቸው ሌላቸውን እንዲረዱ መደላድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡፡ ይህንን ሂደት ለማሳካት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ ተቋማት በሙያቸው፣ በትምህርት ዝግጅታቸው እና ለአጀንዳ ሃሳቦቹ ባላቸው ሙያዊ ቅርበት ብቁ ናቸው ብሎ ያመነባቸው 80 የሚጠጉ የባለሙያዎች ስብስብ (Panel of Experts) በማሰባሰብ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ እያሳተፈ ይገኛል፡፡   የባለሙያዎች ስብስብ በአጀንዳ ነጥቦች ላይ ለሚፈጠሩ ብዥታዎች ማብራሪያ በመስጠት ሂደቱን በመደገፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ በሌላ በኩል በዚህ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለያዩ የሀገር ውስጥ ተቋማት ሂደቱን ለመታዘብ ለኮሚሽኑ ጥያቄ ባቀረቡት መሰረት ከኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጥምረት፣ ከተለያዩ የሙያ ማህበራት፣ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ እና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የተውጣጡ ከ50 በላይ ገለልተኛ ታዛቢዎች የምክክር ሂደቱን እየታዘቡ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
ለባሌ ሮቤ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አጋርፋ ጤና ጣቢያ የሕክምና መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
Jul 21, 2026 63
ሮቤ፣ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ የባሌ ሮቤ አጠቃላይ ሆስፒታልና አጋርፋ ጤና ጣቢያ 200 ሚሊዮን ብር የሚገመት የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገላቸው። ድጋፉን ያደረጉት 'ፕሮጄክት ኪዩር' እና 'ኢስላሚክ ሪሊፍ' የተባሉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች መሆናቸው ተገልጿል። የቁሳቁሶቹን የትራንስፖርት ወጪ በመሸፈን የሶፍ ዑመር የሚኒሶታ ማኅበረሰብ ማኅበር እና መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ድርሻቸውን መወጣታቸው ተገልጿል።   በርክክቡ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ኢሳ ሀሰን (ረዳት ፕሮፌሰር) እንዳሉት፣ ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን ማኅበረሰብ ችግር ለመፍታት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ ነው። በተለይ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ ተግባር በተጓዳኝ በምርምርና ማኅበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።   ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው በሚገኙ የጤና ተቋማት የሕክምና ቁሳቁሶችን ተደራሽ በማድረግ አገልግሎቱን ለማሻሻል የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው የሕክምና ቁሳቁሱ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ውክልናን በመውሰድ፣ የጉምሩክ፣ የግብር እና ሌሎች ተያያዥ ወጪዎችን በመሸፈን ለተጠቃሚው እንዲደርሱ መደረጉን ገልጸዋል። ድጋፉ በሆስፒታሉ የሚታየውን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት በማቃለል ለሕብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ይበልጥ ለማሻሻል ያግዛል ያሉት ደግሞ የባሌ ሮቤ አጠቃላይ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታሁን ኃይሉ ናቸው።   በድጋፍ ከተገኙ የሕክምና መሣሪያዎች መካከል የሕሙማን አልጋ፣ በጽኑ ሕሙማን ክፍል የሚያገለግሉ መሣሪያዎች፣ ማሞቂያ (ኢንኩቤተር)፣ አልትራ ሳውንድ እና ሕሙማን ማመላለሻ የአካል መደገፊያዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል። የሕክምና ቁሳቁሱን ድጋፍ ውጤታማነት ኃላፊነታቸውን ለተወጡ የተቋማት ተወካዮች የዕውቅናና ባህላዊ አልባሳት ተበርክቶላቸዋል።  
ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ህብረተሰቡ በአቅራቢያው የተቀላጠፈ የፍትህ አገልግሎት እንዲያገኝ እያስቻሉ ነው
Jul 21, 2026 69
ሚዛን አማን፣ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ህብረተሰቡ በአቅራቢያው የተቀላጠፈ የፍትህ አገልግሎት እንዲያገኝ እያስቻሉ መሆኑን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፍትህ ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ ቤተልሔም ዳንኤል ለኢዜአ እንዳሉት፥ በ2016 ዓ.ም ተግባራዊ መደረግ የጀመረው የፍትሕ ትራንስፎርሜሽን በክልሉ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል። በዚህም የማህበረሰብ ፍትሕ ላይ በማተኮር 758 ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን አደራጅቶ ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉን ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ብቻ ከ2 ሺህ 400 በላይ መዝገቦች መታየታቸውን አስታውቀዋል። ባህላዊ ፍርድ ቤቶቹ ለህብረተሰቡ በአቅራቢያ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት በመስጠት የጊዜ፣ የጉልበትና የገንዘብን ብክነትን ማስቀረታቸውን ተናግረዋል። በተያዘው አዲስ የበጀት ዓመት ተግባሩን በሁሉም የክልሉ ቀበሌዎች በማስፋፋት ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን መጠን 960 ለማድረስ እንደሚሠራ አስታውቀዋል።   በክልሉ ሞዴል ከሆኑ የቀበሌ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች መካከል በካፋ ዞን ሺሺንዶ ከተማ አስተዳደር የአበች ቀጠና 2 ባህላዊ ፍርድ ቤት ሰብሳቢ ዳኛ መምህር ከበደ ወልደሚካኤል በሕዝቡ በባህላዊው ስርዓት መሰረት ፍርድ እንዲያገኝ እየሰራን ነው ብለዋል። አባቶቻችን ያወረሱንን ሰላም መጠበቂያና ፍትሕ ማስፈኛ እሴት ከመደበኛ የሕግ ሥነ ሥርዓት ጋር በማይጋጭ መልኩ በመቃኘት በቅርበት አገልግሎት እየሰጡ ናቸው ሲሉ ጠቁመዋል። የማህበረሰቡን ፍላጎት መሰረት በማድረግ በቀጣይ የዳኝነት ሥርዓቱን የማስፋፋት ስራ እንደሚከናወን አመላክተዋል። ከተጠቃሚዎች መካከል የሺሺንዳ ከተማ ነዋሪ አቶ ካሳሁን ማሞ መንግስት የፈጠረልን በባህላዊ መንገድ የመዳኘት ምቹ ሁኔታ ፍትሕን ያለ ድካም በቅርበት እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል። በባህላዊ ፍርድ ቤት ሲያደርጉት ለነበረው ክርክር ተገቢውን ውሳኔ ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል።
የሚታይ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፍሪካ ሕብረት የጤና ዘርፍ ጉባኤ ለመሳተፍ ጋና ገቡ
Jul 21, 2026 9
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፦የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፍሪካ ሕብረት የጤና ዘርፍ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ጋና ገብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሙኤል ኦኩዜቶ አብላክዋ እና ሌሎች የሀገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።   የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ልዩ ጉባኤ በጤና ዘርፍ ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚካሄድ ሲሆን፤ በዋናነትም እ.ኤ.አ. በ2030 በአህጉሪቱ ኤች አይ ቪ ኤድስን ከሕብረተሰብ ጤና ስጋትነቱ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ፣ የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞትን መግታት፣ በአህጉሪቱ ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር፣ እንዲሁም የጤና ስርዓቶችን በስትራቴጂካዊ ባለቤትነትና በራስ አቅም ለማጠናከር የሚያስችል ዘላቂ የፋይናንስ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት ላይ ይመክራል።   በጉባኤው የኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ ስኬታማ ተግባራትን ተሞክሮ ለአህጉሪቱ መሪዎች ታካፍላለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጋና በሚኖራቸው ቆይታ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ግንኙነትን ይበልጥ በሚያጠናክሩና ቀጣናዊ ትብብርን በሚያሳድጉ ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመመከት ረገድ የማይተካ ሚናዋን እየተወጣች ነው-አምባሳደር ሃደራ አበራ
Jul 21, 2026 32
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመከላከል ረገድ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት 1354ኛ የሚኒስትሮች ስብሰባውን ዛሬ በበይነ መረብ አካሂዷል።   ስብሰባው በአፍሪካ ሽብርተኝነትና በዓመፅ የታጀበ ጽንፈኝነትን መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል። አምባሳደር ሃደራ አበራ ዓለም አቀፍ የሽብርተኛ ቡድኖች በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት የደቀኑትን ስጋት አንስተዋል። የሽብርተኛ ቡድኖች ዲጂታል አማራጮች እና ማህበራዊ ሚዲያ ጨምሮ ቴክኖሎጂዎችን አባላትን ለመመልመል፣ ፕሮፓጋንዳ ለማሰራጨት እና ጽንፈኝነትን ለማስፋፋት እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ አመልክተዋል።   ዓለም ላይ ያሉ ለውጦችን ከግምት ውስጥ በማስገባት የአፍሪካ ተጠባባቂ ኃይልን ወደ ስራ ማስገባት እና የአፍሪካ ሀገራት በደህንነት እና አስተዳደር ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ አህጉራዊ የአሰራር ማዕቀፎችን በሚገባ መተግበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። አምባሳደር ሃደራ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ሽብርተኝነትን ለመከላከል እና በቀጣናው ያለውን የሽብርተኝነት ነቀርሳ ለማስወገድ እያደረገች ያለውን የማይተካከል አስተዋጽኦ ማንሳታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 107
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ለዓለም ያበረከተችው ታሪካዊ ዕሴት በአርዓያነት የሚጠቀስ ነው 
Jul 21, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ለዓለም ያበረከተችው ታሪካዊ ዕሴት በአርዓያነት የሚጠቀስ መሆኑን የዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ሕብረት (IUCN) የዝርያዎች ሕልውና ኮሚሽን ሊቀመንበር ቪቬክ ሜኖን (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል "60 ዓመታትን ለኢትዮጵያ የዱር ሕይወት" በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በመድረኩ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርና የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን የቦርድ ሰብሳቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።   የዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ሕብረት (IUCN) የዝርያዎች ሕልውና ኮሚሽን ሊቀመንበር ቪቬክ ሜኖን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ ለዓለም ያበረከተችው ታሪካዊ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ባህልና ቅርስ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ታሪክ ጥቂት አሥርተ ዓመታትን ብቻ ሳይሆን በርካታ ክፍለ ዘመናትን ወደ ኋላ የሚመልስ ጥንታዊ መሠረት ያለው መሆኑን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ገና በ15ኛው ክፍለ ዘመን በንጉሥ አፄ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ የመናገሻ ደንን በመጠበቅና በማወጅ የተፈጥሮ ሀብቷን መንከባከብ የጀመረች ሀገር መሆኗን አንስተዋል። ይህም እርምጃ ደኖችና ተፈጥሮ ለዓለም ሕልውና ያላቸውን ከፍተኛ አስፈላጊነት ቀድማ ያወቀችና ጥንታዊ የነቃ አስተዳደርነትን ያሳየች ሀገር መሆኗን ማረጋገጫ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያም ተፈጥሮዋን ለማስጠበቅ እያደረገች ያለችው የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስታውቀዋል። የዱር እንስሳትና ብዝኃ ሕይወት ከሥነ-ምህዳር ጋር ጥብቅ ቁርኝት አላቸው ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ያለ ዝርያዎች ሕልውናና ያለ ብዝኃ ሕይወትሥነ-ምህዳርን በብቸኝነት መጠበቅ እንደማይቻል አስገንዝበዋል። አብዛኞቹ የዓለማችን ድንቅ ፍጥረታት የሚገኙት በምሥራቁ የዓለም ክፍል፣ በተለይም በአፍሪካ እና በእስያ አህጉራት በመሆኑ ዓለም የነዚህን አህጉራት ተፈጥሮ የመጠበቅና የመንከባከብ ከፍተኛ ታሪካዊ ኃላፊነት እንዳለበት አሳስበዋል። የIUCN የዝርያዎች ሕልውና ኮሚሽን በአሁኑ ወቅት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ከ12,000 በላይ ገለልተኛ ሳይንቲስቶችንና ባለሙያዎችን በአባልነት አቅፎ እየሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
ባለሥልጣኑ የዱር እንስሳት ሀብትን በዘላቂነት ለመንከባከብና ዓለምአቀፍ ትብብርን ለማሳደግ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል
Jul 21, 2026 115
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የዝርያ ጥበቃን ለማጠናከር፣ የዱር እንስሳት ሀብትን በዘላቂነት ለመንከባከብና ዓለምአቀፍ ትብብርን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ለአደጋ የተጋለጡ የዱር አራዊትና ዕፅዋት ዝርያዎች ዓለምአቀፍ ንግድ ስምምነት (CITES) ዋና ፀሐፊ ኢቮን ሂጌሮ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል "60 ዓመታትን ለኢትዮጵያ የዱር ሕይወት" በሚል መሪ ሀሳብ በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ፣ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ፣ እንዲሁም አምባሳደሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   ለአደጋ የተጋለጡ የዱር አራዊትና ዕፅዋት ዝርያዎች ዓለም አቀፍ ንግድ ስምምነት (CITES) ዋና ፀሐፊ ኢቮን ሂጌሮ በዚሁ ወቅት፤ ባለሥልጣኑ ባለፉት ዓመታት የዝርያዎች ጥበቃን ለማጠናከር፣ ሕገ-ወጥ የዱር እንስሳት ንግድን ለመከላከልና ዓለም አቀፍ ትብብርን ማሳደግ ያስቻሉ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ1989 ስምምነቱን ከተቀላቀለችበት ጊዜ ጀምሮ ከሴክሬተሪያቱ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ አጋርነት ከፍተኛ አድናቆት እንዳላቸውም ገልጸዋል፡፡ ባለሥልጣኑ በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ፣ በጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ እና በሌሎችም መሠረተ-ልማቶች በሚገኙ የክትትል ጣቢያዎች በኩል ዝሆኖችን ለመቆጣጠር የሚረዳ ጠቃሚ መረጃን ለአለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሲያካፍል ቆይቷል ብለዋል። እነዚህ ስኬቶች የባለሥልጣኑ ሠራተኞች፣ ሬንጀሮችና የአካባቢው ማኅበረሰብ አጋሮች ከአፍሪካ ዝሆን እስከ ጭላዳ ባቡን እና ብርቅዬ እንስሳት ጥበቃ ያደረጉት የማያቋርጥ ጥረት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል። የ2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ትብብር እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመመከት ረገድ የማይተካ ሚናዋን እየተወጣች ነው-አምባሳደር ሃደራ አበራ
Jul 21, 2026 32
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመከላከል ረገድ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት 1354ኛ የሚኒስትሮች ስብሰባውን ዛሬ በበይነ መረብ አካሂዷል።   ስብሰባው በአፍሪካ ሽብርተኝነትና በዓመፅ የታጀበ ጽንፈኝነትን መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል። አምባሳደር ሃደራ አበራ ዓለም አቀፍ የሽብርተኛ ቡድኖች በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት የደቀኑትን ስጋት አንስተዋል። የሽብርተኛ ቡድኖች ዲጂታል አማራጮች እና ማህበራዊ ሚዲያ ጨምሮ ቴክኖሎጂዎችን አባላትን ለመመልመል፣ ፕሮፓጋንዳ ለማሰራጨት እና ጽንፈኝነትን ለማስፋፋት እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ አመልክተዋል።   ዓለም ላይ ያሉ ለውጦችን ከግምት ውስጥ በማስገባት የአፍሪካ ተጠባባቂ ኃይልን ወደ ስራ ማስገባት እና የአፍሪካ ሀገራት በደህንነት እና አስተዳደር ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ አህጉራዊ የአሰራር ማዕቀፎችን በሚገባ መተግበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። አምባሳደር ሃደራ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ሽብርተኝነትን ለመከላከል እና በቀጣናው ያለውን የሽብርተኝነት ነቀርሳ ለማስወገድ እያደረገች ያለውን የማይተካከል አስተዋጽኦ ማንሳታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!
Jul 21, 2026 90
የሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ዐበይት መረጃዎች በትናንትናው ዕለት በቡድን ተከፋፍለው መመካከር የጀመሩት ተመካካሪዎች ዛሬም በየቡድናቸው በመሆን መመካከር ቀጥለዋል፡፡ 50 ተመካካሪዎችን በመያዝ በ80 ቡድን ተከፋፍለው መመካከር የጀመሩት ንዑሳን ቡድኖች በተሟላ ሁኔታ ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ በየንዑስ ቡድናቸው አስር አስር በመሆን ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ሂደት እስከ ነገ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በዚህ ሂደት ተመካካሪዎች በሚመካከሩባቸው የአጀንዳ ሃሳቦች ላይ በርካታ ሃሳቦችን እና ምልከታዎችን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡ሂደቱ ተመካካሪዎች ላለመግባባት መንስኤ የሆኑ እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ አመለካከቶችን እና ምክንያቶችን ከስር መሰረቱ አንዳቸው ሌላቸውን እንዲረዱ መደላድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡፡ ይህንን ሂደት ለማሳካት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ ተቋማት በሙያቸው፣ በትምህርት ዝግጅታቸው እና ለአጀንዳ ሃሳቦቹ ባላቸው ሙያዊ ቅርበት ብቁ ናቸው ብሎ ያመነባቸው 80 የሚጠጉ የባለሙያዎች ስብስብ (Panel of Experts) በማሰባሰብ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ እያሳተፈ ይገኛል፡፡   የባለሙያዎች ስብስብ በአጀንዳ ነጥቦች ላይ ለሚፈጠሩ ብዥታዎች ማብራሪያ በመስጠት ሂደቱን በመደገፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ በሌላ በኩል በዚህ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለያዩ የሀገር ውስጥ ተቋማት ሂደቱን ለመታዘብ ለኮሚሽኑ ጥያቄ ባቀረቡት መሰረት ከኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጥምረት፣ ከተለያዩ የሙያ ማህበራት፣ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ እና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የተውጣጡ ከ50 በላይ ገለልተኛ ታዛቢዎች የምክክር ሂደቱን እየታዘቡ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
ልማትና ዴሞክራሲን ጎን ለጎን በማስኬድ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል
Jul 21, 2026 153
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ልማትና ዴሞክራሲን ጎን ለጎን በማስኬድ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የብሔራዊነት ገዥ ትርክትን ማስረጽና ተቋማዊ አቅምን በማጠናከር ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራም አቶ አደም ፋራህ ተናግረዋል። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።   የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህን ጨምሮ የዋና ጽህፈት ቤት የዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችና ሌሎች አመራሮች እየተሳተፉ ናቸው። አቶ አደም ፋራህ በመድረኩ እንደገለፁት ልማትና ዴሞክራሲን ጎን ለጎን በማስኬድ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። የ2018 በጀት ዓመት በተቋም ግንባታ፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት እና በልማት ሥራዎች ጉልህ ውጤቶች የተመዘገቡበት ዓመት ነው ሲሉም ገልጸዋል። በጀት ዓመቱ ከፓርቲ ግንባታ አኳያ ብልፅግና በአደረጃጀት፣ በአሰራር፣ በሰብዓዊና ቁሳዊ ሀብት እንዲሁም በማስፈጸም አቅሙ ተጠናክሮ የወጣበት ዓመት መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል። በተጨማሪም ድርብርብ ተልዕኮዎችን በታቀደው መሰረት ማሳካት የተቻለበት በጀት ዓመት ነው ብለዋል። መላው ህዝብ በእያንዳንዱ ተልዕኮ ላይ በንቃት እንዲሳተፍ በመደረጉና በባለቤትነት ስሜት ከብልፅግና ፓርቲ ጎን በመቆሙ፣ ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጠንካራ መሰረት የጣለውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ መንታ ግቦች በላቀ አፈጻጸም ማሳካት ተችሏል ነው ያሉት።   ልማትና ዴሞክራሲን ጎን ለጎን በማስኬድ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት የላቀ ውጤት መመዝገቡንም ገልጸዋል። አክለውም የፓርቲውን ግዙፍ አቅም አሟጦ በመጠቀምና የአመራር ሥነ-ምግባር ልህቀትን በማረጋገጥ የሕዝብን ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን ለማድረግ መትጋት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአመራርና አባላትን ጥራት ማረጋገጥ፣ የብሔራዊነት ገዥ ትርክትን ማስረፅ እና የፓርቲውን ተቋማዊ የማዕቀፍ ስታንዳርድ (Standardization) የመገንባት ሥራ በተጠናከረ መንገድ እንደሚከናወን ተናግረዋል። ለዚህም የአመራሩ፣ የአባላቱና የመላው ሕዝብ ርብርብ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል። ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ፤ በ2018 ዓ.ም የአፈጻጸም ሪፖርት እና በ2019 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት የሚደረግ ሲሆን፣ የቀጣይ አቅጣጫዎችም ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ትልቅ ድርሻ አለው
Jul 21, 2026 138
ሆሳዕና፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ለኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ የሚያመጣና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ትልቅ ድርሻ እንዳለው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከህዝብ የሰበሰባቸውን አጀንዳዎች ለይቶ እና አደራጅቶ ለምክክሩ ይፋ ባደረጋቸው አጀንዳዎች ላይ ምክክር እየተካሄደ ይገኛል። የምክክር ሂደቱ የኢትዮጵያን የቆዩ ስብራቶች በማከም የጸናችና ለትውልዱ የምትመች ሀገር ለመገንባት ጠንካራ መሰረት ለማኖር ያስችላል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ሐምሌ 8/2018 ዓም በምክክር ጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት በምክክሩ ከየሰፈራችን ወጥተን ለኢትዮጵያ ስንመክር፣ ለልጆቻችን ስንልና እነርሱን እያሰብን ስንወያይ ውጤቱ ፍሬያማ ይሆናል ማለታቸው ይታወቃል። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን እንዳሉት እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። በዩኒቨርሲቲው የሰላምና ደህንነት ጥናት መምህርና ተመራማሪ ተመስገን ቶማስ (ዶ/ር) አሁን እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ለጋራ ተጠቃሚነት ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። የሀገር እድገትና ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ የዜጎችን የነቃ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ጠቁመው ጎታች አመለካከቶችን በሀገራዊ ምክክሩ በመፍታት ለጋራ ተጠቃሚነት መስራት ይገባል ነው ያሉት። ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ መምከር ለቆዩ ችግሮች የጋራ መፍትሔ ማምጣትና የተዛቡ ትርክቶችን ማረም እንደሚያስችልም ነው የተናገሩት። እየተካሔደ ያለውን ሀገራዊ ምክክር በአግባቡ በመጠቀም ለሀገር እድገትና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መጠቀም ይገባል ብለዋል። የምክክር ሂደቱ ለቆዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄን ይዞ ከመምጣቱ ባለፈ የህዝቦችን አብሮነት በማጠናከር የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ የሚያጠናክር ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩ አበራ ሄቢሶ ናቸው። ለዚህም በኮሚሽኑ ተለይተው የቀረቡ አጀንዳዎች ለቆዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠትና ለተተኪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስተላለፍ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ሲሉ ገልጸዋል። የሚነሱ ችግሮችን በማረም ለሀገረ መንግስት ግንባታው መጠናከር የሚያበረክተው አስተዋጽኦም ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት።
ኢትዮጵያ በልማት እንቅስቃሴዎችና በውጭ ግንኙነት መስክ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበች ትገኛለች
Jul 20, 2026 756
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በልማት እንቅስቃሴዎችና በውጭ ግንኙነት መስክ ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች የሀገሪቱን ሁለተናዊ ብልፅግና ከማረጋገጥ ባለፈ የውሳኔ ሉዓላዊነትን በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውን ምሁራን ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲና ዓለምአቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሤ እንደገለጹት፤ በፖለቲካ ሳይንስና ዲፕሎማሲ መስክ ሉዓላዊነት ሀገራት በውስጣዊም ሆነ በውጭ ጉዳዮቻቸው ላይ ያለማንም ጣልቃ ገብነት በነፃነት የመወሰን ሙሉ ባለቤትነትን ማረጋገጥ መቻል ነው። ከለውጡ በኋላ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ማዕከል ያደረገ የዲፕሎማሲ አካሄድ እየተከተለች እንደምትገኝ ገልፀው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና ወደ ሥራ ማስገባት የመወሰን ነጻነት የታየበት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ሕጋዊና ሞራላዊ መሠረት ያለው የባህር በር የማግኘት ጥያቄን በማንሳት ለዓለም ማህበረሰብ የማስገንዘብ ተግባር እያከናወነች መሆኗም የውሳኔ ሉዓላዊነቷ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። በሀገር ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ሁለተናዊ ዕድገት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ ለአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መጠናከር ያላቸውን ቁልፍ ሚና በግልጽ ያሳያሉ ብለዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ዶክተር መብራቱ አለሙ በበኩላቸው የዲፕሎማሲ አቅም ከሀገር ውስጥ የኢኮኖሚ ጥንካሬ ጋር የተሳሰረ መሆኑን ገልፀዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት መንግስት ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ መግባቱ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የዕዳ ጫናና የዋጋ ንረት ችግሮችን መፍታት ማስቻሉን አንስተዋል። የግል ዘርፉን በማጠናከር፣ የውጭ ባንኮችና ካፒታል ወደ ሀገር እንዲገቡ በር በመክፈትና የካፒታል ገበያን ስርዓትን በመዘርጋት የሀገሪቱን የፋይናንስ አቅም ማሳደጉን ገልፀዋል። በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚም የኤክስፖርት መጠንን በማሳደግና በብድርና በእርዳታ ላይ ያለውን ጥገኝነት በመቀነስ የውሳኔ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በከተሞች በኮሪደር ልማት እየተመዘገበ ያለው ፈጣን እድገት የሀገሪቱን ዓለምአቀፍ ገጽታና የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከልነት እያሳደገ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ማዕከል ያደረገ ባለብዙ ዘርፍ ዲፕሎማሲና ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት መርህን እየተከተለች መሆኗም ለዲፕሎማሲ ስኬቷ መሰረት መሆኑን ምሁራኑ ተናግረዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል
Jul 20, 2026 707
ገንዳ ውሃ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራትን ለማስመዝገብ መቻሉን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። ​የዞኑ አስተዳደር የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ ስራ አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ አካሄዷል።   ​የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት ህዝቡ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት ጥረት የተደረገበት ነው። በተለይም ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ የትምህርትና የጤና ተደራሽነትን የማስፋፋት ተግባራት ተጨባጭ ውጤት የታየባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ውስጥም የተጠናቀቁ የመንገድ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፣ የጤና ተቋማት ግንባታና ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎችን ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል። በአዲሱ በጀት ዓመትም የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል የህዝቡን ጥያቄዎች ሙሉ በሙሉ ለመመለስ መላው አመራርና ህዝቡ በቁርጠኝነት ሊረባረቡ እንደሚገባ አሳስበዋል። ​በብልጽግና ፓርቲ የማእከላዊ ጎንደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እንዳለው ማሩ በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡት ውጤቶች በአመራሩና በአባላቱ የተቀናጀ ጥረት የተገኙ ናቸው ብለዋል።   የተመዘገቡት ውጤቶች የመንግስት መዋቅሩ ፓርቲው በሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሰረት መፈጸም በመቻሉ የመጣ ስኬት መሆኑን ጠቁመው ይህም በአዲሱ በጀት ዓመት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል። ​በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሰብል ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ያሉት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ ጤናው ፋንታሁን ናቸው።   በዚህም በመኸርና በመስኖ ልማት ከ11 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት መቻሉን አውስተዋል። በአዲሱ በጀት ዓመትም የተጀመሩ የግብርና ምርትና ምርታማነት ማሳደጊያ ስራዎችና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በተለየ ትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በመድረኩ የዞኑ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ተመካካሪዎች በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ መምከር ጀምረዋል-ኮሚሽነር መሐሙድ ድሪር
Jul 20, 2026 839
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተመካካሪዎች በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ ዛሬ መምከር መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። የምክክር ጉባኤው ተመካካሪዎች በተለያዩ ቡድኖች ተከፋፍለው በተመደቡበት አጀንዳ ላይ መመካከር መጀመራቸውን ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። ዛሬ የተጀመረው ሂደት የምክክሩ ቁልፍ አካል መሆኑን ጠቅሰው፥ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ በርካታ ሀሳቦች እንደሚንሸራሸሩበት ጠቁመዋል። ኮሚሽኑ ልምድ ያላቸው አመካካሪዎችን በመመደብ የምክክሩን ሂደት እየተከታተለ መሆኑን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም መጀመሩ ይታወቃል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመመከት ረገድ የማይተካ ሚናዋን እየተወጣች ነው-አምባሳደር ሃደራ አበራ
Jul 21, 2026 32
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመከላከል ረገድ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት 1354ኛ የሚኒስትሮች ስብሰባውን ዛሬ በበይነ መረብ አካሂዷል።   ስብሰባው በአፍሪካ ሽብርተኝነትና በዓመፅ የታጀበ ጽንፈኝነትን መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል። አምባሳደር ሃደራ አበራ ዓለም አቀፍ የሽብርተኛ ቡድኖች በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት የደቀኑትን ስጋት አንስተዋል። የሽብርተኛ ቡድኖች ዲጂታል አማራጮች እና ማህበራዊ ሚዲያ ጨምሮ ቴክኖሎጂዎችን አባላትን ለመመልመል፣ ፕሮፓጋንዳ ለማሰራጨት እና ጽንፈኝነትን ለማስፋፋት እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ አመልክተዋል።   ዓለም ላይ ያሉ ለውጦችን ከግምት ውስጥ በማስገባት የአፍሪካ ተጠባባቂ ኃይልን ወደ ስራ ማስገባት እና የአፍሪካ ሀገራት በደህንነት እና አስተዳደር ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ አህጉራዊ የአሰራር ማዕቀፎችን በሚገባ መተግበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። አምባሳደር ሃደራ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ሽብርተኝነትን ለመከላከል እና በቀጣናው ያለውን የሽብርተኝነት ነቀርሳ ለማስወገድ እያደረገች ያለውን የማይተካከል አስተዋጽኦ ማንሳታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!
Jul 21, 2026 90
የሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ዐበይት መረጃዎች በትናንትናው ዕለት በቡድን ተከፋፍለው መመካከር የጀመሩት ተመካካሪዎች ዛሬም በየቡድናቸው በመሆን መመካከር ቀጥለዋል፡፡ 50 ተመካካሪዎችን በመያዝ በ80 ቡድን ተከፋፍለው መመካከር የጀመሩት ንዑሳን ቡድኖች በተሟላ ሁኔታ ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ በየንዑስ ቡድናቸው አስር አስር በመሆን ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ሂደት እስከ ነገ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በዚህ ሂደት ተመካካሪዎች በሚመካከሩባቸው የአጀንዳ ሃሳቦች ላይ በርካታ ሃሳቦችን እና ምልከታዎችን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡ሂደቱ ተመካካሪዎች ላለመግባባት መንስኤ የሆኑ እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ አመለካከቶችን እና ምክንያቶችን ከስር መሰረቱ አንዳቸው ሌላቸውን እንዲረዱ መደላድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡፡ ይህንን ሂደት ለማሳካት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ ተቋማት በሙያቸው፣ በትምህርት ዝግጅታቸው እና ለአጀንዳ ሃሳቦቹ ባላቸው ሙያዊ ቅርበት ብቁ ናቸው ብሎ ያመነባቸው 80 የሚጠጉ የባለሙያዎች ስብስብ (Panel of Experts) በማሰባሰብ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ እያሳተፈ ይገኛል፡፡   የባለሙያዎች ስብስብ በአጀንዳ ነጥቦች ላይ ለሚፈጠሩ ብዥታዎች ማብራሪያ በመስጠት ሂደቱን በመደገፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ በሌላ በኩል በዚህ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለያዩ የሀገር ውስጥ ተቋማት ሂደቱን ለመታዘብ ለኮሚሽኑ ጥያቄ ባቀረቡት መሰረት ከኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጥምረት፣ ከተለያዩ የሙያ ማህበራት፣ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ እና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የተውጣጡ ከ50 በላይ ገለልተኛ ታዛቢዎች የምክክር ሂደቱን እየታዘቡ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
ልማትና ዴሞክራሲን ጎን ለጎን በማስኬድ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል
Jul 21, 2026 153
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ልማትና ዴሞክራሲን ጎን ለጎን በማስኬድ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የብሔራዊነት ገዥ ትርክትን ማስረጽና ተቋማዊ አቅምን በማጠናከር ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራም አቶ አደም ፋራህ ተናግረዋል። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።   የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህን ጨምሮ የዋና ጽህፈት ቤት የዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችና ሌሎች አመራሮች እየተሳተፉ ናቸው። አቶ አደም ፋራህ በመድረኩ እንደገለፁት ልማትና ዴሞክራሲን ጎን ለጎን በማስኬድ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። የ2018 በጀት ዓመት በተቋም ግንባታ፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት እና በልማት ሥራዎች ጉልህ ውጤቶች የተመዘገቡበት ዓመት ነው ሲሉም ገልጸዋል። በጀት ዓመቱ ከፓርቲ ግንባታ አኳያ ብልፅግና በአደረጃጀት፣ በአሰራር፣ በሰብዓዊና ቁሳዊ ሀብት እንዲሁም በማስፈጸም አቅሙ ተጠናክሮ የወጣበት ዓመት መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል። በተጨማሪም ድርብርብ ተልዕኮዎችን በታቀደው መሰረት ማሳካት የተቻለበት በጀት ዓመት ነው ብለዋል። መላው ህዝብ በእያንዳንዱ ተልዕኮ ላይ በንቃት እንዲሳተፍ በመደረጉና በባለቤትነት ስሜት ከብልፅግና ፓርቲ ጎን በመቆሙ፣ ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጠንካራ መሰረት የጣለውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ መንታ ግቦች በላቀ አፈጻጸም ማሳካት ተችሏል ነው ያሉት።   ልማትና ዴሞክራሲን ጎን ለጎን በማስኬድ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት የላቀ ውጤት መመዝገቡንም ገልጸዋል። አክለውም የፓርቲውን ግዙፍ አቅም አሟጦ በመጠቀምና የአመራር ሥነ-ምግባር ልህቀትን በማረጋገጥ የሕዝብን ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን ለማድረግ መትጋት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአመራርና አባላትን ጥራት ማረጋገጥ፣ የብሔራዊነት ገዥ ትርክትን ማስረፅ እና የፓርቲውን ተቋማዊ የማዕቀፍ ስታንዳርድ (Standardization) የመገንባት ሥራ በተጠናከረ መንገድ እንደሚከናወን ተናግረዋል። ለዚህም የአመራሩ፣ የአባላቱና የመላው ሕዝብ ርብርብ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል። ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ፤ በ2018 ዓ.ም የአፈጻጸም ሪፖርት እና በ2019 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት የሚደረግ ሲሆን፣ የቀጣይ አቅጣጫዎችም ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ትልቅ ድርሻ አለው
Jul 21, 2026 138
ሆሳዕና፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ለኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ የሚያመጣና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ትልቅ ድርሻ እንዳለው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከህዝብ የሰበሰባቸውን አጀንዳዎች ለይቶ እና አደራጅቶ ለምክክሩ ይፋ ባደረጋቸው አጀንዳዎች ላይ ምክክር እየተካሄደ ይገኛል። የምክክር ሂደቱ የኢትዮጵያን የቆዩ ስብራቶች በማከም የጸናችና ለትውልዱ የምትመች ሀገር ለመገንባት ጠንካራ መሰረት ለማኖር ያስችላል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ሐምሌ 8/2018 ዓም በምክክር ጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት በምክክሩ ከየሰፈራችን ወጥተን ለኢትዮጵያ ስንመክር፣ ለልጆቻችን ስንልና እነርሱን እያሰብን ስንወያይ ውጤቱ ፍሬያማ ይሆናል ማለታቸው ይታወቃል። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን እንዳሉት እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። በዩኒቨርሲቲው የሰላምና ደህንነት ጥናት መምህርና ተመራማሪ ተመስገን ቶማስ (ዶ/ር) አሁን እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ለጋራ ተጠቃሚነት ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። የሀገር እድገትና ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ የዜጎችን የነቃ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ጠቁመው ጎታች አመለካከቶችን በሀገራዊ ምክክሩ በመፍታት ለጋራ ተጠቃሚነት መስራት ይገባል ነው ያሉት። ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ መምከር ለቆዩ ችግሮች የጋራ መፍትሔ ማምጣትና የተዛቡ ትርክቶችን ማረም እንደሚያስችልም ነው የተናገሩት። እየተካሔደ ያለውን ሀገራዊ ምክክር በአግባቡ በመጠቀም ለሀገር እድገትና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መጠቀም ይገባል ብለዋል። የምክክር ሂደቱ ለቆዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄን ይዞ ከመምጣቱ ባለፈ የህዝቦችን አብሮነት በማጠናከር የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ የሚያጠናክር ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩ አበራ ሄቢሶ ናቸው። ለዚህም በኮሚሽኑ ተለይተው የቀረቡ አጀንዳዎች ለቆዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠትና ለተተኪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስተላለፍ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ሲሉ ገልጸዋል። የሚነሱ ችግሮችን በማረም ለሀገረ መንግስት ግንባታው መጠናከር የሚያበረክተው አስተዋጽኦም ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት።
ኢትዮጵያ በልማት እንቅስቃሴዎችና በውጭ ግንኙነት መስክ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበች ትገኛለች
Jul 20, 2026 756
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በልማት እንቅስቃሴዎችና በውጭ ግንኙነት መስክ ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች የሀገሪቱን ሁለተናዊ ብልፅግና ከማረጋገጥ ባለፈ የውሳኔ ሉዓላዊነትን በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውን ምሁራን ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲና ዓለምአቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሤ እንደገለጹት፤ በፖለቲካ ሳይንስና ዲፕሎማሲ መስክ ሉዓላዊነት ሀገራት በውስጣዊም ሆነ በውጭ ጉዳዮቻቸው ላይ ያለማንም ጣልቃ ገብነት በነፃነት የመወሰን ሙሉ ባለቤትነትን ማረጋገጥ መቻል ነው። ከለውጡ በኋላ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ማዕከል ያደረገ የዲፕሎማሲ አካሄድ እየተከተለች እንደምትገኝ ገልፀው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና ወደ ሥራ ማስገባት የመወሰን ነጻነት የታየበት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ሕጋዊና ሞራላዊ መሠረት ያለው የባህር በር የማግኘት ጥያቄን በማንሳት ለዓለም ማህበረሰብ የማስገንዘብ ተግባር እያከናወነች መሆኗም የውሳኔ ሉዓላዊነቷ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። በሀገር ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ሁለተናዊ ዕድገት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ ለአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መጠናከር ያላቸውን ቁልፍ ሚና በግልጽ ያሳያሉ ብለዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ዶክተር መብራቱ አለሙ በበኩላቸው የዲፕሎማሲ አቅም ከሀገር ውስጥ የኢኮኖሚ ጥንካሬ ጋር የተሳሰረ መሆኑን ገልፀዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት መንግስት ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ መግባቱ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የዕዳ ጫናና የዋጋ ንረት ችግሮችን መፍታት ማስቻሉን አንስተዋል። የግል ዘርፉን በማጠናከር፣ የውጭ ባንኮችና ካፒታል ወደ ሀገር እንዲገቡ በር በመክፈትና የካፒታል ገበያን ስርዓትን በመዘርጋት የሀገሪቱን የፋይናንስ አቅም ማሳደጉን ገልፀዋል። በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚም የኤክስፖርት መጠንን በማሳደግና በብድርና በእርዳታ ላይ ያለውን ጥገኝነት በመቀነስ የውሳኔ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በከተሞች በኮሪደር ልማት እየተመዘገበ ያለው ፈጣን እድገት የሀገሪቱን ዓለምአቀፍ ገጽታና የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከልነት እያሳደገ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ማዕከል ያደረገ ባለብዙ ዘርፍ ዲፕሎማሲና ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት መርህን እየተከተለች መሆኗም ለዲፕሎማሲ ስኬቷ መሰረት መሆኑን ምሁራኑ ተናግረዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል
Jul 20, 2026 707
ገንዳ ውሃ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራትን ለማስመዝገብ መቻሉን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። ​የዞኑ አስተዳደር የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ ስራ አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ አካሄዷል።   ​የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እያሱ ይላቅ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት ህዝቡ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት ጥረት የተደረገበት ነው። በተለይም ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ የትምህርትና የጤና ተደራሽነትን የማስፋፋት ተግባራት ተጨባጭ ውጤት የታየባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ውስጥም የተጠናቀቁ የመንገድ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፣ የጤና ተቋማት ግንባታና ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎችን ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል። በአዲሱ በጀት ዓመትም የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል የህዝቡን ጥያቄዎች ሙሉ በሙሉ ለመመለስ መላው አመራርና ህዝቡ በቁርጠኝነት ሊረባረቡ እንደሚገባ አሳስበዋል። ​በብልጽግና ፓርቲ የማእከላዊ ጎንደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እንዳለው ማሩ በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡት ውጤቶች በአመራሩና በአባላቱ የተቀናጀ ጥረት የተገኙ ናቸው ብለዋል።   የተመዘገቡት ውጤቶች የመንግስት መዋቅሩ ፓርቲው በሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሰረት መፈጸም በመቻሉ የመጣ ስኬት መሆኑን ጠቁመው ይህም በአዲሱ በጀት ዓመት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል። ​በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሰብል ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ያሉት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ ጤናው ፋንታሁን ናቸው።   በዚህም በመኸርና በመስኖ ልማት ከ11 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት መቻሉን አውስተዋል። በአዲሱ በጀት ዓመትም የተጀመሩ የግብርና ምርትና ምርታማነት ማሳደጊያ ስራዎችና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በተለየ ትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በመድረኩ የዞኑ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ተመካካሪዎች በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ መምከር ጀምረዋል-ኮሚሽነር መሐሙድ ድሪር
Jul 20, 2026 839
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተመካካሪዎች በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ ዛሬ መምከር መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። የምክክር ጉባኤው ተመካካሪዎች በተለያዩ ቡድኖች ተከፋፍለው በተመደቡበት አጀንዳ ላይ መመካከር መጀመራቸውን ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። ዛሬ የተጀመረው ሂደት የምክክሩ ቁልፍ አካል መሆኑን ጠቅሰው፥ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ በርካታ ሀሳቦች እንደሚንሸራሸሩበት ጠቁመዋል። ኮሚሽኑ ልምድ ያላቸው አመካካሪዎችን በመመደብ የምክክሩን ሂደት እየተከታተለ መሆኑን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም መጀመሩ ይታወቃል።
ማህበራዊ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፍሪካ ሕብረት የጤና ዘርፍ ጉባኤ ለመሳተፍ ጋና ገቡ
Jul 21, 2026 9
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፦የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፍሪካ ሕብረት የጤና ዘርፍ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ጋና ገብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሙኤል ኦኩዜቶ አብላክዋ እና ሌሎች የሀገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።   የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ልዩ ጉባኤ በጤና ዘርፍ ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚካሄድ ሲሆን፤ በዋናነትም እ.ኤ.አ. በ2030 በአህጉሪቱ ኤች አይ ቪ ኤድስን ከሕብረተሰብ ጤና ስጋትነቱ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ፣ የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞትን መግታት፣ በአህጉሪቱ ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር፣ እንዲሁም የጤና ስርዓቶችን በስትራቴጂካዊ ባለቤትነትና በራስ አቅም ለማጠናከር የሚያስችል ዘላቂ የፋይናንስ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት ላይ ይመክራል።   በጉባኤው የኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ ስኬታማ ተግባራትን ተሞክሮ ለአህጉሪቱ መሪዎች ታካፍላለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጋና በሚኖራቸው ቆይታ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ግንኙነትን ይበልጥ በሚያጠናክሩና ቀጣናዊ ትብብርን በሚያሳድጉ ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ለባሌ ሮቤ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አጋርፋ ጤና ጣቢያ የሕክምና መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
Jul 21, 2026 63
ሮቤ፣ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ የባሌ ሮቤ አጠቃላይ ሆስፒታልና አጋርፋ ጤና ጣቢያ 200 ሚሊዮን ብር የሚገመት የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገላቸው። ድጋፉን ያደረጉት 'ፕሮጄክት ኪዩር' እና 'ኢስላሚክ ሪሊፍ' የተባሉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች መሆናቸው ተገልጿል። የቁሳቁሶቹን የትራንስፖርት ወጪ በመሸፈን የሶፍ ዑመር የሚኒሶታ ማኅበረሰብ ማኅበር እና መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ድርሻቸውን መወጣታቸው ተገልጿል።   በርክክቡ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ኢሳ ሀሰን (ረዳት ፕሮፌሰር) እንዳሉት፣ ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን ማኅበረሰብ ችግር ለመፍታት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ ነው። በተለይ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ ተግባር በተጓዳኝ በምርምርና ማኅበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።   ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው በሚገኙ የጤና ተቋማት የሕክምና ቁሳቁሶችን ተደራሽ በማድረግ አገልግሎቱን ለማሻሻል የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው የሕክምና ቁሳቁሱ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ውክልናን በመውሰድ፣ የጉምሩክ፣ የግብር እና ሌሎች ተያያዥ ወጪዎችን በመሸፈን ለተጠቃሚው እንዲደርሱ መደረጉን ገልጸዋል። ድጋፉ በሆስፒታሉ የሚታየውን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት በማቃለል ለሕብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ይበልጥ ለማሻሻል ያግዛል ያሉት ደግሞ የባሌ ሮቤ አጠቃላይ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታሁን ኃይሉ ናቸው።   በድጋፍ ከተገኙ የሕክምና መሣሪያዎች መካከል የሕሙማን አልጋ፣ በጽኑ ሕሙማን ክፍል የሚያገለግሉ መሣሪያዎች፣ ማሞቂያ (ኢንኩቤተር)፣ አልትራ ሳውንድ እና ሕሙማን ማመላለሻ የአካል መደገፊያዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል። የሕክምና ቁሳቁሱን ድጋፍ ውጤታማነት ኃላፊነታቸውን ለተወጡ የተቋማት ተወካዮች የዕውቅናና ባህላዊ አልባሳት ተበርክቶላቸዋል።  
ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ህብረተሰቡ በአቅራቢያው የተቀላጠፈ የፍትህ አገልግሎት እንዲያገኝ እያስቻሉ ነው
Jul 21, 2026 69
ሚዛን አማን፣ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ)፦ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ህብረተሰቡ በአቅራቢያው የተቀላጠፈ የፍትህ አገልግሎት እንዲያገኝ እያስቻሉ መሆኑን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፍትህ ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ ቤተልሔም ዳንኤል ለኢዜአ እንዳሉት፥ በ2016 ዓ.ም ተግባራዊ መደረግ የጀመረው የፍትሕ ትራንስፎርሜሽን በክልሉ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል። በዚህም የማህበረሰብ ፍትሕ ላይ በማተኮር 758 ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን አደራጅቶ ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉን ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ብቻ ከ2 ሺህ 400 በላይ መዝገቦች መታየታቸውን አስታውቀዋል። ባህላዊ ፍርድ ቤቶቹ ለህብረተሰቡ በአቅራቢያ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት በመስጠት የጊዜ፣ የጉልበትና የገንዘብን ብክነትን ማስቀረታቸውን ተናግረዋል። በተያዘው አዲስ የበጀት ዓመት ተግባሩን በሁሉም የክልሉ ቀበሌዎች በማስፋፋት ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን መጠን 960 ለማድረስ እንደሚሠራ አስታውቀዋል።   በክልሉ ሞዴል ከሆኑ የቀበሌ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች መካከል በካፋ ዞን ሺሺንዶ ከተማ አስተዳደር የአበች ቀጠና 2 ባህላዊ ፍርድ ቤት ሰብሳቢ ዳኛ መምህር ከበደ ወልደሚካኤል በሕዝቡ በባህላዊው ስርዓት መሰረት ፍርድ እንዲያገኝ እየሰራን ነው ብለዋል። አባቶቻችን ያወረሱንን ሰላም መጠበቂያና ፍትሕ ማስፈኛ እሴት ከመደበኛ የሕግ ሥነ ሥርዓት ጋር በማይጋጭ መልኩ በመቃኘት በቅርበት አገልግሎት እየሰጡ ናቸው ሲሉ ጠቁመዋል። የማህበረሰቡን ፍላጎት መሰረት በማድረግ በቀጣይ የዳኝነት ሥርዓቱን የማስፋፋት ስራ እንደሚከናወን አመላክተዋል። ከተጠቃሚዎች መካከል የሺሺንዳ ከተማ ነዋሪ አቶ ካሳሁን ማሞ መንግስት የፈጠረልን በባህላዊ መንገድ የመዳኘት ምቹ ሁኔታ ፍትሕን ያለ ድካም በቅርበት እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል። በባህላዊ ፍርድ ቤት ሲያደርጉት ለነበረው ክርክር ተገቢውን ውሳኔ ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ17 አደገኛ የወንጀል ቡድን አባላት የምርመራ መዝገብ ለፍትሕ ሚኒስቴር ላከ
Jul 21, 2026 197
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ17 አደገኛ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውሎ የምርመራ መዝገብ በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማደራጀት ለፍትሕ ሚኒስቴር መላኩን አስታወቀ። ፖሊስ እንደገለጸው በምሥራቅ ሀገራችን በኩል በጂቡቲ እና በየመን አድርገው ወደ ሳውዲ አረቢያ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ ሲልኩ የቆዩና ከተጎጂዎች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ የተቀበሉ፣ በአደገኛ ሕገ-ወጥ አዘዋዋሪ መሐመድ ጣሂር አደን (ወርዲ) የሚመሩ የተደራጁ 17 የወንጀል ቡድን አባላትን በቁጥጥር ሥር አውሎ የምርመራ መዝገብ በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማደራጀት ለፍትሕ ሚኒስቴር ልኳል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባሰባሰበው የሰው እና የሰነድ ማስረጃ ተጠርጣሪዎቹ በሰው ልጅ ለመነገድ በማሰብ የወንጀል ቡድን በማደራጀት በወንጀል ድርጊቱ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ መሳተፋቸውን በምርመራ መዝገቡ ማጣራቱን ገልጿል። ተጠርጣሪዎቹ የሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር መረብ በመዘርጋት፣ ተጎጂዎቹ በየመን በኩል ወደ ሳውዲ አረቢያ ገብተው የተሻለ ኑሮ እንደሚኖሩ ሐሰተኛ ተስፋ በመስጠትና በማሳመን ከተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች በደላሎች አማካኝነት ተጎጂዎችን በመመልመል ሲልኩ መቆየታቸውንም ፖሊስ አረጋግጧል። በምርመራ መዝገቡ እንደተመለከተው በሕገ-ወጥ መንገድ የተወሰዱ ተጎጂዎች የኢትዮጵያን ድንበር እንደተሻገሩ ወደ የመን ተወስደው በየመን ሀገር ውስጥ በሚገኙ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጁ መጋዘኖች ታጉረው ከፍተኛ ኢሰብአዊ ድርጊቶች ይፈጸሙባቸው ነበር። በተለይም ተጠርጣሪዎቹ ተጎጂዎችን በመያዣነት በመያዝ ወደ ቤተሰቦቻቸው ስልክ በማስደወል ከፍተኛ ገንዘብ ሲጠይቁ እንደነበር እና ገንዘብ መክፈል ላልቻሉ ቤተሰቦች ተጎጂዎችን እየደበደቡ እንዲሁም እያሰቃዩ ቪዲዮ በመቅረጽ የሥነልቦና ጫና ሲፈጥሩ እንደነበር ፖሊስ አረጋግጧል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፍትህ ሚኒስቴር፣ ከብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ባደረገው ጠንካራ ክትትልና ምርመራ በርካታ ከባባድ ግኝቶችን ይፋ አድርጓል። ከእነዚህም መካከል ሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎቹ ከተጎጂዎች ከ1 ቢሊየን ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ መቀበላቸውን፣ ከ40,000 በላይ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ ማዘዋወራቸውን፣ ከ60 ሰዎች በላይ ለሕልፈተ ህይወት መዳረጋቸው እንዲሁም በርካታ ሴቶች መደፈራቸው በምርመራ ተደርሶባቸዋል። በዚህ ወንጀል ጉዳይ በርካታ ሰዎች የምስክርነት ቃላቸውን የሰጡ ሲሆን፣ ከሳውዲ አረቢያ እና ከኢትዮጵያ በቀጥታ መስመር በቪዲዮ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል። ተጠርጣሪዎቹ በሕገ-ወጥ መንገድ ያገኙትን ከፍተኛ ገንዘብ በመጠቀም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት ማፍራታቸውን ፖሊስ ያረጋገጠ ሲሆን በስማቸው የነበረ ቤት፣ ተሽከርካሪ እና ገንዘብ እንዲታገድ አድርጓል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በሰው የመነገድ፣ በሕገወጥ ሀዋላ እና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር (Money Laundering) ወንጀሎች ምርመራውን አጠናቆ ለፍትሕ ሚኒስቴር መላኩን አስታውቋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋናውን እያቀረበ፤ ኅብረተሰቡ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp)፣ 991 ነፃ የስልክ መስመር እና ሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ (SPS)ን በመጠቀም መረጃ በመስጠት ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አስተላልፏል።
ኢኮኖሚ
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 107
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተካሄዱ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ሆነናል
Jul 21, 2026 72
ከሚሴ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፡-ባለፉት የለውጥ ዓመታት ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በከሚሴ ከተማ "የኢትዮጵያ ከተሞች የኮሪደር ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው ስለ ኢትዮጵያ የተሰኘ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።   በምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የከሚሴ ከተማ ነዋሪ ሼህ የሱፍ ይማም እንደገለፁት፣ በለውጡ ዓመታት በተቀናጀ መንገድ ሰላምን ከማስፈን ባሻገር ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ሆነናል። ከለውጡ በፊት ከተማዋ በልማት ወደ ኋላ የቀረች ከመሆኑ በተጨማሪ ግጭቶች የሚታዩባት እንደነበር አስታውሰዋል። አሁን ላይ የተሟላ ሰላም ከመሰፈኑ ባሻገር በከተማዋ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶች መሟላታቸው ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።   ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ የባቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ኡመር መሐመድ በበኩላቸው፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚሰሩ የልማት ስራዎች ማሕበረሰቡ ለረዥም ጊዜ ሲያነሳቸው ለነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ናቸው። በተለይም የአካባቢውን ሰላም ከማጽናት ባለፈ የዲጂታል አገልግሎት በተሻለ ጥራት ተደራሽ በማድረግ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል። የአካባቢያችን ሰላም ተጠብቆ በተሰሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ ሆነናል ያሉት ደግሞ የጨፋ ሮቢት ከተማ ነዋሪ አቶ አሊ ሰይድ ናቸው።   ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከአጎራባች ዞኖችና ክልሎች ጋር ያለንን ግንኙነት በማጠናከር በልማት ጭምር መተሳሰሩ ይበልጥ እንድንቀራረብና በጋራ ተጠቃሚ መሆን እንድችል አድርጓል ነው ያሉት። የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ህብረተሰቡን በማሳተፍ ሰላምን ለማስፈን በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት ። ከሰላም ማስክበር ስራው በተጓዳኝ የህዝቡን የልማት ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎችን በማከናወን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደተቻለ ገልፀዋል።   በመድረኩ የከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒን ጨምሮ የፌዴራል ፣ የክልል ፣ የዞንና የከተማ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በዞኑ ህብረተሰቡን በቅርበት ለማገልገል ወደ ተግባር የገቡ የቀበሌ አደረጃጀቶች ለልማት ስራዎች ምቹ ሁኔታ ፈጥረዋል
Jul 21, 2026 68
ጊምቢ፣ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን ህብረተሰቡን በቅርበት ለማገልገል ወደ ተግባር የገቡ የቀበሌ አደረጃጀቶች የተሟላ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ለልማት ስራዎች ምቹ ሁኔታ እንደፈጠሩላቸው ነዋሪዎች ገለጹ። አደረጃጀቱ በቅርበት የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማስቻሉም በላይ፣ ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድጉ የተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲከናወኑ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሚገኝ የዞኑ ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት ነዋሪዎች መካከል የጊምቢ ከተማ 01 ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ አስካለ ሕርጳ፤ የቀበሌ አደረጃጀቱ የመንግሥት አገልግሎትን በቅርበት ከማግኘታቸው በላይ በአካባቢያቸው የተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲከናወኑ አስችሏል፡፡ በተለይም አደረጃጀቱ ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ በአካባቢያቸው የነበረውን የጸጥታ ችግር መቅረፍ መቻሉን ጠቅሰው፤ አመራሮቹ በየጊዜው ከህብረተሰቡ ጋር በመቀራረብ ይስተዋሉ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። የመንዲ ከተማ የቀርሳ ዋልጋ ቀበሌ ነዋሪ አቶ በላይ መልካሙ በበኩላቸው፣ የተዘረጋው አደረጃጀት ተጠቃሚነታቸውን ያሳደጉ የተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲከናወኑ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም በአካባቢያቸው ሰላም እንዲሰፍን ከማድረጉም በላይ የቆዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲቀረፉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። አሁን የተዘረጋው የቀበሌ አደረጃጀት ጉዳያቸውን ለማስፈጸም ወደተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ከማመልከትና ከመንገላታት እንደታደጋቸው የተናገሩት ደግሞ አቶ አያና ገላልቻ ናቸው። ከዚህ ቀደም ከመሬት ወሰን ይዞታ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ለማስፈጸም ለተለያዩ እንግልቶች ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን በአዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ ማስፈጸም መቻላቸውን ጠቅሰዋል። አደረጃጀቱ በስራ ላይ መዋሉ ውስብስብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታትና ሠላም እንዲሰፍን በማድረግ በኩል አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል። የቀበሌ አደረጃጀቱ ቀልጣፋ፣ ዘመናዊ እና ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለህብረተሰቡ በቅርበት መስጠት ማስቻሉን የተናገሩት ደግሞ የጊምቢ ከተማ 01 ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ ሙሊጌታ አደሙ ናቸው። በአደረጃጀቱ ህብረተሰቡን በማቀናጀት በአካባቢው የነበረውን የጸጥታ ችግር በመቅረፍ ሰላም እንዲሰፍን ተድርጓል ብለዋል። በቀጣይም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየትና ተደራሽ የሆኑ አገልግሎቶችን በማሳለጥ የህዝብ ጥያቄዎችን አግባብ ባለው መንገድ ለመፍታት በተቀናጀ መልኩ እንደሚሰራ አመላክተዋል።   የምዕራብ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ እንደተናገሩት በዞኑ 464 የቀበሌ አደረጃጀቶች ተደራጅተው ለሕዝቡ በቅርበት አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል። አደረጃጀቱ በተለይም በዞኑ ይስተዋሉ የነበሩ የፀጥታ ችግሮችን በመቅረፍ ሂደት ህብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር እንዲሰራ እድል ፈጥሯል ብለዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን የዞኑ ህዝብ ለረጅም ጊዜ ሲያነሳቸው የነበሩ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ፈጥኖ ለመመለስ እድል መፍጠሩንም አስረድተዋል።  
በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል
Jul 21, 2026 99
ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ በ2018/19 የምርት ዘመን 393 ሺህ 600 ሄክታር መሬት በሩዝ ሰብል ለመሸፈን ታቅዶ እስካሁን ከ370 ሺህ ሄክታር በላይ የመሬት ዝግጅት መደረጉን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሚፍታህ ጋሊ ተናግረዋል። በዞኑ 19 ወረዳዎች ሩዝ የሚለማ መሆኑን የገለጹት አቶ ሚፍታህ ባለፈው የምርት ዘመን ከ14 ሚሊዮን 800 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም ምርታማነቱን ለማስፋፋት ምርጥ ዘር የማባዛት ሥራ እየተከናወነ ሲሆን በዞኑ በሚገኙ የኅብረት ሥራ ዩኒየኖች አማካይነት ስኬታማ ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል። በዘንድሮ ዓመት በጅማ ዞን ቀርሳ ወረዳ የኅብረት ሥራ ዩኒየን በኩል 50 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ምርጥ ዘር ተባዝቶ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ያለ ብክነት ተሰብስቧል ነው ያሉት። ይህም ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የሩዝ ሰብል ምርጥ ዘር በሀገር ውስጥ ለማምረት ታቅዶ እየተሠራ በመሆኑ ነው ብለዋል።   ከዚህ በተጨማሪም በሩዝ ሰብል ልማት ላይ ለበርካቶች የሥራ ዕድል ተፈጥሮ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው ብለዋል። በጅማ ዞን ቀርሳ ወረዳ በኅብረት ሥራ ዩኒየን በዘር ማባዛት ሥራ ላይ ተሰማርተው ባገኙት የሥራ ዕድል ውጤታማ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ ሲራጅ ጀማል እና ዛኪር አባራያ ናቸው። ዞኑ ምቹ የአየር ጠባይ ያለው እንደመሆኑ በየጊዜው የተሻለ ምርት እየተሰበሰበ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ሥራ ላይ ከተሰማሩ በኋላ ሕይወታቸው እየተሻሻለ መሆኑን ገልጸው ከዚህ በተጨማሪም ባላቸው መሬት ላይ በማምረት ተጠቃሚ መሆናቸውን አክለዋል። ወጣት ከድር አባዝናብ፤ ዩኒየኑ የሩዝ ሰብል ምርጥ ዘርን ለማስፋፋት እያከናወነ በሚገኘው የግብርና ሥራ ተሰማርቶ ከራሱ አልፎ ቤተሰቡን እያገዘ መሆኑን ጠቅሷል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በክልሉ የወጣቶችን የፈጠራ ችሎታ ለሚያጎለብቱ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቷል
Jul 20, 2026 654
ጅግጅጋ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፦በሶማሌ ክልል የወጣቶችን የፈጠራ ችሎታና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን የሚያጎለብቱ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ አስታወቁ። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ የክልሉን ኢኖቬሽን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ የወጣቶችን የፈጠራ ችሎታና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማጎልበት አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመንና የዲጂታል ኢኮኖሚን ለማሳለጥ ትኩረት ተሰጥቷል። በዚህም የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው የክልሉ የኢኖቬሽን ማዕከልም በቴክኖሎጂ ብቁ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት እና በዘርፉ አቅማቸውን ለማጠናከር ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። መንግሥት ለቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ልማት የሰጠው ትኩረት አበረታች ለውጦች እያስመዘገበ መሆኑን ጠቁመው ይህንኑ ለማስፋት እየተሠራ ነው ሲሉ አክለዋል። በቀጣይም ማዕከሉን የማስፋት፣ በግብአትና፣ በሙያተኞች የማጠናከር ስራ በትኩረት እንደሚከናወን አመላክተዋል። የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ መሀመድ አሊ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ የወጣቶችን የፈጠራ ችሎታና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅም የሚገነባና ክህሎታቸውን የሚያጎለብት መሆኑን ተናግረዋል። ማእከሉ የ2030 የዲጂታል እቅድ ስትራቴጂን ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ጠቁመው ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ የተቋቋመ መሆኑን ተናግረዋል።   ማዕከሉ በድረገጽ ልማት፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በመረጃ ትንተና፣ ሳይበር ሴኩሪቲ፣ ዲጂታል ዲዛይን አገልግሎት በመሳሰሉት ስልጠና የሚሰጥበት መሆኑን ተናግረዋል። ማዕከሉ በተጨማሪም አነስተኛ ንግዶችን የማልማትና የምርምር አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል። በስነ ስርአቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ ወጣቶች፣ የፈጠራ ባለሙያዎች፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ የማቋቋም ርዕይ ሀገሪቱን የአፍሪካ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል ያደርጋታል
Jul 20, 2026 712
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ (AIU) የማቋቋም ርዕይ ሀገሪቱን የአፍሪካ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል የሚያደርግ ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን የአፍሪካ ኅብረት የትምህርት ክፍል ኃላፊ ሶፊያ አሺፓላ ገለጹ። ኢትዮጵያ የጀመረችውን ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ ዲጂታል ቴክኖሎጂን የኢኮኖሚ ምሰሶና የልማት ማሳለጫ መሣሪያ በማድረግ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበች ትገኛለች። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂና የአምስት ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ መርሐ ግብርም የዜጎችን የዲጂታል፣ የሰው ሠራሽ አስተውሎትና የዳታ ሳይንስ ዕውቀትና ክህሎት የሚያበለጽግ አቅም እየፈጠሩ ነው። የዲጂታላይዜሽን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የመንግሥት አገልግሎቶችን ጥራትና ተደራሽነት በማረጋገጥ በቁልፍ የኢኮኖሚ መሣሪያነት በማገልገል ስኬት አስገኝቷል። የአፍሪካ ኅብረት የትምህርት ክፍል ኃላፊ ሶፊያ አሽፓላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ቴክኖሎጂ መስክ ወሳኝ መደላድል በመፍጠር አበረታች ውጤት እያመጣች ነው። በተለይም የሰው ሠራሽ አስተውሎትን ልማት ለማፋጠን ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የወሰደችው ተነሳሽነት ከፍተኛ አድናቆት የሚቸረው መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የተጀመረው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ልማት አብዮትም በሌሎች የአፍሪካ አገራት ተመሳሳይ ኢንቨስትመንቶች እንዲስፋፉ በር የሚከፍት ታሪካዊ ክስተት እንደሆነ አንስተዋል። ይህም በአፍሪካ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ልማት የለውጥ ጉዞ ላይ ትልቅ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ የማቋቋም ርዕይ የወደፊቱን ትምህርትና ምርምር በተሻለ ጥራት በመቅረጽ አገሪቱን ፈር ቀዳጅ እንደሚያደርጋት አስረድተዋል። ይህም የሰለጠነና ብቁ የሰው ኃይል በማፍራት፣ በአፍሪካ የፈጠራ፣ የምርምርና የሰው ኃይል ልማትን የሚያፋጥን ዓለም አቀፍ የልማት አብዮት መሆኑን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ የትምህርት መሠረተ ልማትን የማስፋፋት ተግባር የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ለአፍሪካ አገራት ጭምር በአርአያነት የሚወሰድ መሆኑን አስገንዝበዋል። በአንደኛና በቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ውጤታማነትም ሕፃናትንና ታዳጊዎችን በተሻለ ዕውቀትና ክህሎት በማበልጸግ ሀገር ተረካቢ ዜጋን ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ የመንግስት አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ውጤታማ ስራ እየተሰራ ነው
Jul 20, 2026 115
ባህር ዳር፤ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የመንግስት አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ የታገዙ በማድረግ ስኬታማ ስራዎች ማከናወን መቻሉን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ የቻለ ይግዛው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የነበረውን ስራ አፈፃፀም አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ፤ የመንግስት አሰራሮችን በቴክኖሎጂ በማዘመን የላቀ አገልግሎት ለመስጠት ተችሏል። በተለይም ከለውጡ ዓመታት ወዲህ ቴክኖሎጂን በማዘመን በኩል የተሰጠው ልዩ ትኩረት ዘርፉ በፍጥነት እንዲያድግና ውጤታማ እንዲሆን ማስቻሉን ተናግረዋል። ለዚህም የቴክኖሎጂ የእውቀት ክፍተትን በስልጠና ለመሙላት፣ የፈጠራ አቅምን ለማሳደግ እና በዘርፉ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመዝለቅ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መሰጠቱን ገልፀዋል። በክልሉ ከ725 ሺህ በላይ ወገኖችን ለማሰልጠን ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ ሲሆን በሁለት ዙር ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ወገኖችን ስልጠናውን መውሰዳቸውን ተናግረዋል። በዘርፉ ስኬታማ ስራዎችን ለማከናወን የተቻለው በየደረጃው የሚገኘው አመራር በልዩ ቁርጠኝነት ስራዎችን ለማከናወን በመቻሉ ነው ብለዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ወገኖችን የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ባለቤት ማድረግ እንደተቻለ አመልክተዋል። በአዲሱ በጀት ዓመትም በገጠርና በከተማ 12 ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች የዲጅታል መታወቂያን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ከዚህ ባለፈም የተቋማትን አገልግሎትን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ከእጅ ንክኪ የራቀ ለማድረግም በዋና ዋና ከተሞች የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም በክልል ደረጃም በባህር ዳር፣ ደሴና ወልዲያ ከተሞች አገልግሎቱን በማስጀመር የህዝብ ቅሬታዎችን መፍታት መቻሉን ገልፀዋል። በክልል ደረጃ በተቋቋመው መሶብ የአንድ ማዕከል ቀደም ሲል ተደጋጋሚ ቅሬታ ይቀርብባቸው የነበሩ በ15 ተቋማት 65 አገልግሎቶችን መስጠት መቻሉን አስገንዝበዋል። በቀጣይም በጎንደር፣ ደብረ ታቦር ፣ ደብር ብርሃንና ኮምቦልቻ ከተሞች አገልግሎቱን ለማስፋት የግንባታና ሌሎች ቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አብራርተዋል። ቴክኖሎጂን ማስፋፋት የህዝብን እንግልትና ድካም የሚቀንሱ አሰራሮችን ይበልጥ በማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አንስተው፤ ለውጤታማነቱ ሁሉም በላቀ ቅንጅት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።  
በክልሉ የዳኝነት አገልግሎትን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው
Jul 20, 2026 236
አዳማ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ጋዛሊ አባሲማል ገለጹ።   በ6ኛው የጨፌ ኦሮሚያ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቧል። ሪፖርቱን ያቀረቡት የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ ጋዛሊ አባሲማል፤ በክልሉ ፍትሐዊና ተደራሽ የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል። በዚህም የፍርድ ቤቶች የማስፈጸም አቅም ከመጨመሩ ባሻገር መዝገቦች ሳይጓተቱ በተቀመጠላቸው ጊዜ ውስጥ ተመርምረው ውሳኔ እንዲያገኙ መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል። በተለይም የዳኝነት አገልግሎትን በቪዲዮ ኮንፈረንስ ማካሄድ ባለጉዳዮች ከሩቅ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ በመደረጉ የባለጉዳዮችን እንግልትና ወጪ ማስቀረት እንደተቻለ ገልጸዋል።   ዜጎች ካሉበት ሆነው የፍትሕ ሂደቱን እንዲከታተሉና ምስክር እንዲያሰሙ በተዘረጋው የቴክኖሎጂ ሥርዓት ከ181 ሺህ በላይ የክስ መዝገቦች ላይ ውሳኔ ማግኘታቸውንም ጠቅሰዋል። ከዚህም ባለፈ የሐሰት ማስረጃዎች በተወሰነ መልኩ እየቀነሱ መምጣታቸውን ገልጸው፣ የሥነ-ምግባር ችግር ባለባቸው ዳኞች ላይም እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አስረድተዋል። በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 318 የሕግ ጥሰትና የዳኝነት ሥነ-ምግባር ጉድለት በፈጸሙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን ጨምሮ የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ በበጀት ዓመቱ ከ500 ሺህ በላይ መዝገቦች ላይ ውሳኔ በመስጠት የዓመታዊ ዕቅዱን 97 በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል። በሌላ በኩል፣ በክልሉ በሥራ ላይ የሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች እየሰጡ ባሉት አገልግሎቶች በመደበኛ ፍርድ ቤቶች ላይ የነበረው ጫና ከመቀነሱ ባለፈ አለመግባባቶች በሀገር በቀል እሴት መፍትሔ እንዲያገኙ ሆኗል ብለዋል። በተመሳሳይ ሴቶች፣ ሕፃናትና አቅመ ደካሞች ነፃ የሕግ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት።  
ስፖርት
ስፔን አርጀንቲናን በመርታት የዓለም ዋንጫን አነሳች
Jul 20, 2026 222
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ግብ ሳይቆጠርበት በአቻ ውጤት ተጠናቋል። የአርጀንቲና የአማካይ ተጫዋች ኤንዞ ፈርናንዴዝ በ93ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በ90 ደቂቃ አሸናፊ ባለመገኘቱ ቡድኖቹ ወደ ጭማሪ ሰዓት አምርቷል። ተቀይሮ የገባው ፌራን ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በጨዋታው ስፔን ፍጹም የበላይነት ወስዳለች። የአርጀንቲናው ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ በርካታ ያለቀላቸው ኳሶችን አድኗል። ተጋጣሚዋ አርጀንቲና በጨዋታው ደካማ እንቅስቃሴ አድርጋለች። ቡድኑ የግብ እድል መፍጠር ተስኖታል። ውጤቱን ተከትሎ ስፔን ለሁለተኛው የዓለም ዋንጫን አንስታለች። አውሮፓዊቷ ሀገር እ.አ.አ በ2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 19ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ እንደነበረች ይታወሳል። አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ ክብሯን ማስጠበቅ አልቻለችም። ለአራተኛ ጊዜ ዋንጫ የማንሳት ህልሟ አልተሳካም።
“ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ” ታላቁ ሩጫ በሐረር ከተማ ተካሄደ
Jul 19, 2026 210
ሀረር ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ “ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018” የ10 ኪሎ ሜትር ታላቁ ሩጫ ውድድር በሐረር ከተማ ተካሄደ። በውድድሩ በተለያየ የዕድሜ ክልል ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ አትሌቶች፣ ተጋባዥ እንግዶች፣ የውጪ አገር ቱሪስቶች፣ አርቲስቶችን ጨምሮ በርካታ ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል። ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ የሩጫ ውድድር ቀደም ሲል በደብረብርሃን፣ ሀዋሳ፣ ጅማ፣ አርባ ምንጭና በቆጂ ከተሞች የተካሄደ ሲሆን የፍጻሜ ውድድሩ ዛሬ በሐረር ከተማ ተካሂዷል።   በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ በተካሄደው የታላቁ ሩጫ ውድድርን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መክዩ መሀመድና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተው አስጀምረዋል። በ10 ኪሎ ሜትር በተካሄደው በዚህ ውድድር በወንዶች ሴና ገመቹ ሲያሸንፍ፤ ምህረት አወቀና ኢብራሂም መሀመድ በቅደም ተከተል 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል። በሴቶች ራሔል እምቢበል ስታሸንፍ አምረን ሸምሱና አዚዛ መሀመድ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን አግኝተዋል።   በሁለቱም ጾታ ከተደረገው የአትሌቶች ውድድር በተጨማሪ በአዋቂዎች፣ በወጣቶች፣ በታዳጊ ሕጻናትና በሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በሁለቱም ጾታዎች የ5 ኪሎ ሜትር ውድድር ተከሂዷል። ውድድሩን ላሸነፉ ተወዳዳሪዎች የተዘጋጀላቸውን የማበረታቻ ሽልማት ከእለቱ የክብር እንግዳ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መክዩ መሀመድ አበርክተዋል።   “ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018” ታላቁ ሩጫ ውድድር ቱሪዝም ሚኒስቴር እና ታላቁ ሩጫ በኢትዮዽያ በመተባበር ያዘጋጁት የጎዳና ላይ ውድድር መሆኑ ተገልጿል። ውድድሩ በሕዝቦች መካከል አብሮነትን የማጠናከር፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የማሳደግ እንዲሁም አዲስ የስፖርት መነቃቃትን የመፍጠር ዓላማ እንዳለውም ተመላክቷል።
አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ ክብሯን ታስጠብቃለች ወይስ ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ዳግም አሸናፊ ትሆናለች?
Jul 19, 2026 452
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን እና አርጀንቲና ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ የዓለም አይኖች አርፈውበታል። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም ይካሄዳል። ስፔን በግማሽ ፍጻሜው ለዋንጫ ታልፋለች ተብላ የተጠበቀችውን ፈረንሳይን 2 ለ 0 በመርታት በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ ለፍጻሜ ቀርባለች። የወቅቱ የዋንጫ ባለቤት አርጀንቲና እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለተከታታይ ሁለት የዓለም ዋንጫዎች ለፍጻሜ ደርሳለች። አርጀንቲና ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስታልፍ የአሁኑ ለሰባተኛ ጊዜ ነው። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም በዓለም ዋንጫው አንድ ጊዜ ተገናኝተዋል። እንግሊዝ እ.አ.አ በ1966 ባዘጋጀችው ስምንተኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በምድብ ሁለት ተገናኝተው አርጀንቲና 2 ለ 1 አሸንፋለች። ሉዊስ አርቲም ለአርጀንቲና ሁለቱን ግቦች አስቆጥሯል። ፒሪ የስፔንን ጎል በወቅቱ ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ሀገራቱ በውድድር እና ወዳጅነት ጨዋታዎች 14 ጊዜ ተጫውተው በተመሳሳይ ስድስት ጊዜ ድል ቀንቷቸዋል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ስፔን በ14ቱ ጨዋታዎች ላይ 22 ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ አርጀንቲና 18 ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። እ.አ.አ በ2018 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 19ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ስፔን ብቸኛ ክብሯን ያገኘችበት ነው። ተጋጣሚዋ አርጀንቲና ከዚህ ቀደም ስድስት ጊዜ ለፍጻሜ ደርሳ ሶስቱን በማሸነፍ በውድድሩ ስኬታ ከሚባሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። አርጀንቲና የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈች ከጀርመን እና ጣልያን ጋር በተመሳሳይ አራት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳች ሀገር ትሆናለች። በተጨማሪም የደቡብ አሜሪካ ሀገር ከጣልያን እና ብራዚል በመቀጠል ዓለም ዋንጫን በተከታታይ ያነሳች ሀገር ለመሆን ትጫወታለች። ሌላኛው ትኩረት የሳበው ጉዳይ ሀገራቱ የየአህጉራቸው ውድድሮች የወቅቱ አሸናፊ መሆናቸው ነው። ስፔን የአውሮፓ ዋንጫ፣ አርጀንቲና የኮፓ አሜሪካ አሸናፊ ናቸው። የአውሮፓ እና የደቡብ አሜሪካ ቁንጮዎች የሚያደርጉት ፍልሚያ ትኩረትን ስቧል። አውሮፓዊቷ ስፔን እ.አ.አ በ2010 የዓለም ዋንጫን ከማንሳቷ በፊት የ2008 የአውሮፓ ዋንጫ አሸናፊ ነበረች። ስፔን የወቅቱ የአውሮፓ ዋንጫ ባለቤት ሆና ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ መቅረቧ ገጠመኙን የተለየ አድርጎታል። በዘንድሮው ዓለም ዋንጫ ድንቅ ብቃቱን እያሳየ የሚገኘው ሊዮኔል ሜሲ በዛሬው ጨዋታ ልዩ ትኩረት አግኝቷል። የ39 ዓመቱ ሜሲ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ስምንት ጎሎችን በማስቆጠር እና አራት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል ከኪሊያን እምባፔ (10 ጎሎች ሲያስቆጥር እና አራት የግብ እድሎችን ፈጥሯል) በኮከብ ግብ አግቢነቱ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በዓለም ዋንጫው 21 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ በምንጊዜውም የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ዝርዝር ውስጥ በእምባፔ አንድ ጎል ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ሜሲ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ለማጠናቀቅ እና የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መሪነት ይዞ ለመቀጠል ሁለት ግቦችን ማስቆጠር እና ለግብ የሚሆን ኳስ ማቀበል ይጠበቅበታል። አርጀንቲናዊው ኮከብ በዓለም ዋንጫ በርካታ ጨዋታዎችን በማድረግ (33) እና በርካታ ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል (12) የክብረ ወሰን ባለቤት ነው። እድሜው በገፋበት ሰዓት እያሳየ ያለው ብቃት አድናቆት እንዲጎርፍለት አድርጓል። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አንድ ግብ ያስቆጠረው የ18 ዓመቱ ላሚን ያማል ከስፔን በኩል ትኩረት የተሰጠው ተጫዋች ነው። ስፔን በጨዋታው ላይ የኳስ ቁጥጥርን መሰረት ያደረገ እና የክንፍ መስመር የማጥቃት እንቅሰቃሴ ላይ ያተኮረ የአጨዋወት ስልት ወደ ሜዳ ይዛ ትገባለች ተብሎ ይጠበቃል። ተጋጣሚዋ አርጀንቲና የተደራጀ የመከላከል ቅርጽ በመያዝ ኳስ ሲያገኙ በፈጣን መልሶ ማጥቃት ግብ የማስቆጠር አጨዋወትን ትከተላለች ተብሎ ይጠበቃል። ጨዋታው ጠንካራ እና በታክቲክ የታጠረ እንደሚሆን ይጠበቃል። የ46 ዓመቱ ስሎቬኒያዊ ስላቫኮ ቪንቺች ተጠባቂውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። አሸናፊው ሀገር ከዋንጫው በተጨማሪ የ50 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ያገኛል። ሁለተኛ የሚወጣው ቡድን የ33 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይበረከትለታል። የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) አጠቃላይ በውድድሩ ላይ ለተሳተፉ ሀገራት የ871 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት አዘጋጅቷል።   አሜሪካዊው ዝነኛ ድምጻዊና ራፐር ፖስት ማሎን (Post Malone) የዓለም ዋንጫው የመዝጊያ ስነ ስርዓት ዋና አቅራቢ (Headline Performer) ነው። ከእሱ በተጨማሪ ሮቢ ዊሊያምስ፣ ኒኮል ሸርዚንገር እና ላውራ ፓውሲኒ የተባሉ ታዋቂ ድምጻውያን እንዲሁም ታዋቂው ዩቲዩበር አይሾው ስፒድ (IShowSpeed) በዝግጅቱ ላይ የሚሳተፉ ሲሆን፣ የሆሊውድ ተዋናዩ ቶም ክሩዝም ልዩ እንግዳ ሆኖ ይቀርባል። በእረፍት ሰዓት (Halftime Show) ላይ ደግሞ ማዶና፣ ሻኪራ፣ ጀስቲን ቢበር፣ ቢቲኤስ (BTS) እና በርና ቦይ ከኮልድ ፕለይ (Coldplay) ጋር በመሆን በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚቀርበው የእረፍት ሰዓት ትዕይንት ላይ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ። በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት ከሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ሲካሄድ የቆየው 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ፍጻሜውን ያገኛል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ለዓለም ያበረከተችው ታሪካዊ ዕሴት በአርዓያነት የሚጠቀስ ነው 
Jul 21, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ለዓለም ያበረከተችው ታሪካዊ ዕሴት በአርዓያነት የሚጠቀስ መሆኑን የዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ሕብረት (IUCN) የዝርያዎች ሕልውና ኮሚሽን ሊቀመንበር ቪቬክ ሜኖን (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል "60 ዓመታትን ለኢትዮጵያ የዱር ሕይወት" በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በመድረኩ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርና የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን የቦርድ ሰብሳቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።   የዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ሕብረት (IUCN) የዝርያዎች ሕልውና ኮሚሽን ሊቀመንበር ቪቬክ ሜኖን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ ለዓለም ያበረከተችው ታሪካዊ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ባህልና ቅርስ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳትና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ታሪክ ጥቂት አሥርተ ዓመታትን ብቻ ሳይሆን በርካታ ክፍለ ዘመናትን ወደ ኋላ የሚመልስ ጥንታዊ መሠረት ያለው መሆኑን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ገና በ15ኛው ክፍለ ዘመን በንጉሥ አፄ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ የመናገሻ ደንን በመጠበቅና በማወጅ የተፈጥሮ ሀብቷን መንከባከብ የጀመረች ሀገር መሆኗን አንስተዋል። ይህም እርምጃ ደኖችና ተፈጥሮ ለዓለም ሕልውና ያላቸውን ከፍተኛ አስፈላጊነት ቀድማ ያወቀችና ጥንታዊ የነቃ አስተዳደርነትን ያሳየች ሀገር መሆኗን ማረጋገጫ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያም ተፈጥሮዋን ለማስጠበቅ እያደረገች ያለችው የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስታውቀዋል። የዱር እንስሳትና ብዝኃ ሕይወት ከሥነ-ምህዳር ጋር ጥብቅ ቁርኝት አላቸው ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ያለ ዝርያዎች ሕልውናና ያለ ብዝኃ ሕይወትሥነ-ምህዳርን በብቸኝነት መጠበቅ እንደማይቻል አስገንዝበዋል። አብዛኞቹ የዓለማችን ድንቅ ፍጥረታት የሚገኙት በምሥራቁ የዓለም ክፍል፣ በተለይም በአፍሪካ እና በእስያ አህጉራት በመሆኑ ዓለም የነዚህን አህጉራት ተፈጥሮ የመጠበቅና የመንከባከብ ከፍተኛ ታሪካዊ ኃላፊነት እንዳለበት አሳስበዋል። የIUCN የዝርያዎች ሕልውና ኮሚሽን በአሁኑ ወቅት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ከ12,000 በላይ ገለልተኛ ሳይንቲስቶችንና ባለሙያዎችን በአባልነት አቅፎ እየሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ እያበረከተችው ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው
Jul 21, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ እያበረከተችው ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት የብዝሃ ሕይወት ስምምነት (CBD) አስፈጻሚ ጸሀፊ አስትሪድ ሾማከር ገለጹ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ ነው፡፡ በመድረኩ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርና የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን የቦርድ ሰብሳቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። የተባበሩት መንግሥታት የብዝሃ ሕይወት ስምምነት (CBD) አስፈጻሚ ጸሀፊ አስትሪድ ሾማከር ፣ ኢትዮጵያ የበርካታ፣ ልዩ የእፅዋትና የእንስሳት ዝርያዎች መገኛና የብዝሃ ሕይወት ማዕከል መሆኗን ተናግረዋል። ሀገሪቱ ለዓለም አቀፍ የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ እያበረከተች ያለው ሚና እጅግ ጉልህ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በዓለም ላይ በሌላ ቦታ የማይገኙ ብርቅዬ ዝርያዎች ባለቤት መሆኗን ጠቅሰው፤ ይህ ልዩ የተፈጥሮ ቅርስ ለኢትዮጵያ ኩራት ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም ሊተመን የማይችል እሴት እንዳለው ተናግረዋል። ባለፉት ስድስት አስርት ዓመታት የተፈጥሮና የብዝሃ ሕይወት ቅርሶችን ለመጠበቅ ተቋሙ ላሳየው ቁርጠኝነትም አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ሀገሪቱ የጥበቃ ቦታዎችን በሚገባ በማስተዳደር፣ አደጋ ላይ ያሉ ዝርያዎችን በመታደግ እና በሰውና በዱር እንስሳት መካከል የሚፈጠሩ ግጭቶችን ለመቆጣጠር ያደረገችው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን አብራርተዋል። የተቀመጡ የብዝሃ ሕይወት ግቦችን ስኬታማ ለማድረግ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የደን ሀብትን በመጠበቅ፣ ዝርያዎችን ከአደጋ ለመታደግ እና ሕገወጥ የዱር እንስሳት ንግድን ለመቆጣጠር የተፋጠነ እርምጃ መውሰድ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ባለሥልጣኑ የዱር እንስሳት ሀብትን በዘላቂነት ለመንከባከብና ዓለምአቀፍ ትብብርን ለማሳደግ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል
Jul 21, 2026 115
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የዝርያ ጥበቃን ለማጠናከር፣ የዱር እንስሳት ሀብትን በዘላቂነት ለመንከባከብና ዓለምአቀፍ ትብብርን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ለአደጋ የተጋለጡ የዱር አራዊትና ዕፅዋት ዝርያዎች ዓለምአቀፍ ንግድ ስምምነት (CITES) ዋና ፀሐፊ ኢቮን ሂጌሮ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል "60 ዓመታትን ለኢትዮጵያ የዱር ሕይወት" በሚል መሪ ሀሳብ በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ፣ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ፣ እንዲሁም አምባሳደሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   ለአደጋ የተጋለጡ የዱር አራዊትና ዕፅዋት ዝርያዎች ዓለም አቀፍ ንግድ ስምምነት (CITES) ዋና ፀሐፊ ኢቮን ሂጌሮ በዚሁ ወቅት፤ ባለሥልጣኑ ባለፉት ዓመታት የዝርያዎች ጥበቃን ለማጠናከር፣ ሕገ-ወጥ የዱር እንስሳት ንግድን ለመከላከልና ዓለም አቀፍ ትብብርን ማሳደግ ያስቻሉ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ1989 ስምምነቱን ከተቀላቀለችበት ጊዜ ጀምሮ ከሴክሬተሪያቱ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ አጋርነት ከፍተኛ አድናቆት እንዳላቸውም ገልጸዋል፡፡ ባለሥልጣኑ በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ፣ በጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ እና በሌሎችም መሠረተ-ልማቶች በሚገኙ የክትትል ጣቢያዎች በኩል ዝሆኖችን ለመቆጣጠር የሚረዳ ጠቃሚ መረጃን ለአለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሲያካፍል ቆይቷል ብለዋል። እነዚህ ስኬቶች የባለሥልጣኑ ሠራተኞች፣ ሬንጀሮችና የአካባቢው ማኅበረሰብ አጋሮች ከአፍሪካ ዝሆን እስከ ጭላዳ ባቡን እና ብርቅዬ እንስሳት ጥበቃ ያደረጉት የማያቋርጥ ጥረት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል። የ2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ትብብር እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን በመጠበቅ የዱር ሕይወት መጠጊያና መኖሪያ የሚያገኙበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል
Jul 21, 2026 161
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን በመጠበቅ የዱር ሕይወት መጠጊያና መኖሪያ የሚያገኙበትን ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን የኢፌድሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል "60 ዓመታትን ለኢትዮጵያ የዱር ሕይወት" በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ለዘመናት ያከማቸችውን የዱር ሕይወት ጥበቃ ከትውልድ ወደ ትውልድ በማሸጋገር ከአፍሪካ ግንባር ቀደም እንደሚያደርጋት ገልጸዋል። የኢትዮጵያውያን የዱር ሕይወት ጥበቃ ባህላዊ ሥርዓትም ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ አስደናቂ ዕሴት መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት መለያ የሆነው የዋሊያ አይቤክስ መመናመን አሳሳቢ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ይህንን ለመታደግ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ግዴታ አለብን ብለዋል። በአንዳንድ አካባቢዎች በአጉል ልማድና ኋላ ቀር አስተሳሰብ በመነሳት በዱር እንስሳት ላይ የሚደርሰውን ጥፋት በማስቆም ጸጋዎችን አጥብቆ መያዝ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ የተፈጥሮ ሀብቶችንና የብዝኃ ሕይወት ሥነ-ምህዳር ሚዛንን ለመጠበቅ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም የደረቁ ምንጮችንና ደኖችን በመመለስ ሸሽተውና ጠፍተው የነበሩ የዱር እንስሳት መጠጊያና መኖሪያነት እያገለገሉ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም በአጭር ጊዜ ውስጥ የታየ እውነታ መሆኑን በማንሳት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሁለንተናዊ ስኬት እንዲመዘገብ በማስቻል ለብዝኃ ሕይወት ደኅንነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። ቀደም ሲል ከነበረው ልማዳዊ አሠራር ሰንሰለት በመላቀቅ በብሔራዊ ፓርኮች ልማት አዲስ ሕይወትና እይታ ለመስጠት የተደረገው ርብርብ ትልቅ እመርታ ማምጣቱንም ጠቁመዋል። የፓርኮችን ደኅንነት ማረጋገጥ እና መሠረተ ልማቶቻቸውን ማዘመን ለዱር ሕይወት ጥበቃ ብቻ ሳይሆን የሀገር ውስጥ እና የውጭ ጎብኚዎችን ለመሳብ ለሚደረገው ጥረት ቁልፍ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል። በከተሞች እየተገነቡ ያሉ ፓርኮችም ሕብረተሰቡ ለዱር ሕይወት ያለውን የእውቀት አድማስ የሚያሰፉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዘርፉ የሚጠበቀውን ውጤት ለማምጣት ተግቶ መስራት እንደሚገባ ጠቁመው፤ ባለፉት ስልሳ ዓመታት ባለሥልጣኑ እንዲሁም አጋር አካላት ተፈጥሮን ለመጠበቅ ላበረከቱት ጉልህ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በመድረኩ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርና የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን የቦርድ ሰብሳቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 20144
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 13050
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 11846
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 11744
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 107
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ስብራትን የጠገነ፤ ተስፋንም ያለመለመ በጎነት
Jul 20, 2026 163
የበጎነት ኃይል፤ የአቶ ጥላሁን አበበና ቤተሰቡ አዲስ የሕይወት ምዕራፍ በታደሰችው አዲስ አበባ ሰማይ ሥር በበጎነት ሲገለጥ!! "እንኳን ደስ አለዎት፤ ቤትዎ ደርሷል፤ በሰላም ይግቡ!!" አቶ ጥላሁን አበበ ይህን ዜና በሰሙበት ቅጽበት ለጥቂት ደቂቃዎች መናገር አልቻሉም። በዐይናቸው ተቋጥሮ በጉንጫቸው የሚወርደው እንባ የደስታ ብቻ አልነበረም። የዓመታት መከራ፣ የተበተነ ቤተሰብ፣ በሸራ ሥር የተደረገ የሕይወት ትንቅንቅና በተስፋ ብቻ የተገፋ ሕይወት ሁሉ በአንድ ቅጽበት በፊታቸው ተደቀነ። ዛሬ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ የልጆቻቸው ሳቅ ይሰማል። የቤቱ ግድግዳ የድህነትን ጩኸት በደስታ ቀይሮታል። ይህ የተገነባው ቤት ብቻ ሳይሆን፣ የተሰበረ ልብና ተስፋም ጭምር ነው። የሕይወት ፈተና፡- አቶ ጥላሁን በ1963 ዓ.ም. በአማራ ክልል ደሴ ዙሪያ አማራ ሳይንት ተወለዱ። ልጅነታቸውን እንደ ብዙ የገጠር ልጆች ሁሉ በጨዋታ፣ በከብት እረኝነትና በፈረስ ግልቢያ አሳለፉ። ነገር ግን በ12 ዓመታቸው ከፈረስ ላይ በወደቁበት አደጋ የሕይወታቸውን መንገድ ቀየሩት። በዚህም ቀኝ እጃቸው ከባድ ጉዳት አስተናገደ። ከዚያ በኋላ የአካል ጉዳተኝነት የዕለት ተዕለት ሕይወታቸው ሆነ። ይህ ብቻ አልበቃ አለ። በዚያ የለጋነት ዕድሜያቸው እናታቸውን በሞት አጡ። ቤተሰባቸውም ሌላ ፈተና ውስጥ ወደቀ። በዚያ ዕድሜ ብዙዎች ተስፋ ይቆርጣሉ፤ እርሳቸው ግን የያዙት ተስፋ ነበር። "እጄን ለልመና ከመዘርጋት ይልቅ በሥራዬ መኖር ይገባኛል" የሚለው ጽኑ ሃሳባቸው በ1979 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ አመጣቸው። ከተማዋ ማንንም በቀላሉ አትቀበልም። በተለይ አንድ እጁን ያጣ ወጣት ለመኖር እጅግ ፈታኝ ነበር። ሆኖም የቻሉትን ሁሉ ሠሩ፤ በአንድ እጃቸው ሕይወትን ለማሸነፍ ቀንና ሌሊት ታገሉ። የሰቀቀኑ ዘመን፡- ትዳር መሠረቱ፤ የአምስት ልጆች አባት ሆኑ። ነገር ግን የመኖሪያ ቤት እጦት የቤተሰቡን ደስታ በእጅጉ መፈታተኑን ቀጠለ። ይህ የብዙዎች የዘመናት እጣ ፈንታ ነበር። አቶ ጥላሁንም የዚሁ ሰለባ ሆኑ። አንዳንዴ ልጆቹ ዘመድ ቤት ያድሩ ነበር። አንዳንዴም ወደ ገጠር ይላካሉ። እርሳቸውም በሚሠሩበት ቦታ ሁሉ ሸራ ዘርግተው ያድራሉ። ለአንድ አባት ከልጆቹ ጋር አብሮ አለመኖር ከማንኛውም ድህነት በላይ የሚከብድ ነው። የቤት ተስፋ ግን አልጠፋም። ስማቸውን በብዙ የአዲስ አበባ የወረዳና የቀበሌ መስተዳድሮች አስመዘገቡ። ዓመታትን ጠበቁ፤ በትዕግሥትም ኖሩ።   ተስፋ የለመለመበት ምዕራፍ፡- ተስፋ ያለመለመው በጎነት እንዲሉ፣ 2015 ዓ.ም. ለአቶ ጥላሁንና ለቤተሰባቸው አዲስ የሕይወት ምዕራፍን የከፈተችበትን አጋጣሚ ፈጠረች። በአዲስ አበባ ከተማ በበጎ ፈቃድና በማኅበራዊ ድጋፍ መርሃ ግብሮች አማካኝነት የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ሆኑ። "ምስጋና ለፈጣሪ ይሁን። ይህ በጎ ተግባር ከነበርኩበት ማኅበራዊ ቀውስ አውጥቶ ብሩህ ሕይወት እንድመራ አስችሎኛል" ሲሉ የሚናገሩት ቃላቸው ከልባቸው ነው። ምክንያቱም የተበተነው ቤተሰባቸው ዳግም በአንድ ጣሪያ ሥር ተሰብስቧል፤ የተሰበረ ልባቸውና ተስፋቸውም ተጠግኗል።   ባለቤታቸው ወይዘሮ ዓይናለም ታረቀኝ እንደሚሉት፤ የቤቱ መገኘት ቤተሰቡን እንደገና ወልዶታል። "ከዚህ በፊት ልጆቻችን ተበታትነው ነበር፤ አሁን ግን አብረን እንኖራለን። የነበረው ጭንቀት ቀርቷል፤ ሕይወታችንም ተቀይሯል" ይላሉ። ልጃቸው አክሊሉ ጥላሁንም የልጅነት ትዝታውን ሲያስታውስ፣ "አባቴን በሥራ ቦታው እየተከተልኩ ብዙ መከራ አይቻለሁ። ዛሬ ግን አንድ ቤት ውስጥ መኖራችን ትልቅ ደስታ ነው" ይላል። በጎነት የሕይወት ትርጉም ነው፡- የአቶ ጥላሁን ታሪክ የአንድ ሰው ታሪክ ብቻ አይደለም፤ እንደ ዋርካ በገነኑ ሕንፃዎች ግርጌ የዘመሙ ጎጆዎች ታሪክም ጭምር እንጂ። የበጎነት ኃይል የሰውን ሕይወት በብርሃን ፍጥነት ይቀይራል። የአቶ ጥላሁን ቤተሰብ የሕይወት ዑደትም ሕያው ምስክር ነው። በጎነት ግድግዳ ብቻ አትገነባም፤ የተሰበረን ተስፋና ልብን ታድሳለች። የተበተነን ቤተሰብ ታሰባስባለች። የአቶ ጥላሁን ቤት የተገነባው በሲሚንቶና በጡብ ብቻ አይደለም፤ በመረዳዳት፣ በአብሮነትና ሰውን ሰው አድርጎ በማየት ነው።   በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማኅበረሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ምክትል ኮሚሽነር አስራት ንጉሴ እንደሚገልጹት፣ በበጎ ፈቃድ የሚከናወኑ ተግባራት የበርካታ ዜጎችን ችግር ከመቅረፍ ባሻገር፣ የኢትዮጵያውያንን የመረዳዳትና የአብሮነት እሴት እያጠናከሩ ይገኛሉ። እንደ አቶ ጥላሁን ያሉ ታሪኮችም የዚህ እውነታ ሕያው ምስክሮች ናቸው። በጎነት እጅ ሲዘረጋ የሚቀየረው የአንድ ሰው ኑሮ ብቻ አይደለም። የአንድ ቤተሰብ እጣ ፈንታ፣ የአንድ ማኅበረሰብ ተስፋና የአንድ ሀገር የአብሮነት መንፈስም ጭምር ነው። የዚህ ታሪክ ትልቁ ትምህርትም ይኸው ነው። አንድ የበጎነት እጅ ለአንድ ሰው ቤት ብቻ አይሰጥም፤ የነገን ሕይወትም ይገነባል። በጎነታችን ለአብሮነታችን፣ አብሮነታችን ለተሻለ ተስፋችን!  
ምክክር ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት
Jul 20, 2026 127
ረጅም ታሪክ፣ቱባ ባህልና ሕብረ-ብሔራዊነት መለያዋ የሆኑት ኢትዮጵያ፣ የነገ ተስፋዋን አስተማማኝ ለማድረግ አዲስ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል ይበልጥ ብሩህ ለማድረግ ሀገራዊ ምክክር ቁልፍና ታሪካዊ ሚና ይጫወታል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በመላ ሀገሪቱ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ አጀንዳዎችን የመሰብሰብ አጠናቆ ዋናውን ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በይፋ ማካሄድ ጀምሯል። ኮሚሽኑ በመላ ሀገሪቱ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡትን ሀሳቦችን በማደራጀት ለዋናው ሀገራዊ ምክክር በቀረቡት ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ምክክር እየተካሄደ ነው። የተለዩትን መሠረታዊ አጀንዳዎች መነሻ በማድረግ የሚደረገው ውይይት፣የፖለቲካ መረጋጋትን ከመፍጠር ባለፈ ለአስተማማኝ የኢኮኖሚ እድገትና ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። ምክክሩ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ያለው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው።ባለፉት የታሪክ ሂደቶች የተፈጠሩ ቅሬታዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በሰላማዊ ውይይት በመፍታት፣እርስ በርስ ለመደማመጥ እና ታሪካዊ ቁስሎችን በይቅርታ ለመፈወስ የሚያስችል ዋነኛ መንገድ ነው። ከጠመንጃና ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሀሳብ የበላይነት የሚነግስበትን፣አለመግባባቶችና ልዩነቶች በሰላማዊ ውይይትና በንግግር የሚፈቱበትን ባህል ያሰፍናል።ይህም ልዩነቶችን በመቀበል በአንድነትና በጋራ መኖር የሚያስችሉ የጋራ እሴቶችና ሀገራዊ መግባባቶች ለማጠናከር ይረዳል። ከዚህም ባለፈ፣ምክክሩ ለተቋማዊ እድገትና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዋነኛ ምሰሶ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ መልካም አጋጣሚን ይፈጥራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በተከፈተበት እለት ባስተላለፉት መልዕክት፥ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ኢትዮጵያ በገዛ እጇ አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የሚያስችላትን “ብዕርና ብራና” ያገኘችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ሲሉ ገልጸውታል። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፣ አብረን ተስፋን፣ ይቅርታን እና በጋራ መኖርን እንትከል፤ በሀገር ውስጥ በሚደረግ ውይይትና ይቅርታ ችግሮቻችንን በመፍታት ሀገራችንን ከውጭ ጣልቃ ገብነት እንጠብቅ በማለት አሳስበዋል። ተሳታፊዎች በሙሉ ለኢትዮጵያ መልካም፣ ለአፍሪካ አስተማሪ፣ ለመላው ኢትዮጵያውያን ደግሞ እውነተኛ እረፍትን የሚያመጣ ታሪካዊ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል። ይህንን በጎ ዕድል ለመጠቀምም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንነትና በኃላፊነት ስሜት በመሳተፍ ለሀገር ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ሀገራዊ ምክክር የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል በራስ አቅምና ጥበብ ለመወሰን የሚያስችል ትልቅ እድል ነው።የኢትዮጵያ መጻኢ ተስፋና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ጋር የተሳሰረ ነው። ባለፉት የታሪክ ሂደቶች ውስጥ የተፈጠሩ ቅሬታዎችን በንግግር መፍታት፣ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሃሳብ የበላይነት የሚነግስበትን ምቹ መደላድል ይፈጥራል። ዛሬ በምክክሩ ጠረጴዛ ዙሪያ የሚታየው የመነጋገር እና የመደማመጥ ባህል እንዲሁም ችግሮችን በውይይት ብቻ የመፍታት አማራጭ የተሻለች ኢትዮጵያን እውን የሚያደርግ ታሪካዊ መሰረት ይጥላል።
ክልሎችን በወፍ በረር
Jul 19, 2026 150
ሀምሌ ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ክልሎችን በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉አማራ ክልል የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ። ለ30 ዓመታት ያህል ተቋርጦ የነበረው የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ በዘመናዊ መልክ ተገንብቶ በይፋ ተመርቋል። አወሮፕላን ማረፊያው 2 ሺህ 400 ሜትር ርዝመትና 30 ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን፣ እንደ Q400 እና B737 ያሉ ግዙፍ የሕዝብና የጭነት አውሮፕላኖችን ማሳረፍ ይችላል። ይህም የአካባቢውን ንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ያነቃቃል ተብሏል። በምርቃ መርሃ ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፌዴራል እና የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ታድመዋል። 👉ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል "ትምህርት ለልጄ" የክረምት ንቅናቄ መካሄድ። በትምህርት ቤቶች ደረጃንና የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ያለመ የ2018 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ንቅናቄ መድረክ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ተካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተማሪዎች ብቁ ሆነው እንዲወጡ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻልና ግብዓት በማሟላት ረገድ በትኩረት መሠራቱን ገልጸዋል። 👉ድሬዳዋ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲዎችን በትክክለኛ መረጃ ላይ መስርቶ ለመቅረጽ የሚያስችል የዲጂታል ሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ሥርዓት በድሬዳዋ ተጀምሯል። ተግባሩ የተከናወነው በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት እና በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ሲሆን የተቋማቱ ዋና ዳይሬክተሮች ሰላማዊት ዳዊት እና ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ይህ ሥርዓት የ"ዲጂታል 2030" ትግበራ አካል ነው። 👉ሶማሌ ክልል ሰብዓዊ መብትና ሰላም ግንባታ ጉዞ። ‘ሰብዓዊ መብትና የሰላም ግንባታ’ በሚል መሪ ሐሳብ አገር አቀፍ የጸጥታና ፍትሕ አካላት ጉባኤ በጅግጅጋ ከተማ ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ የተጠርጣሪዎችና የታራሚዎች አያያዝ መሻሻል ማሳየቱን የጠቀሱ ሲሆን፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ በበኩላቸው በክልሉ ለሰላም፣ ለጸጥታና ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። 👉ሲዳማ ክልል የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ስኬት- የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ (CBE) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ውድድር አሸናፊ ለሆነው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ በየነ በራሳ የክለቡ ውጤት የአንድነትና የትጋት ማሳያ መሆኑን ገልጸው፣ ይህንን ስኬት በአርአያነት በመውሰድ በሌሎች የልማት መስኮችም መድገም እንደሚገባ አሳስበዋል። 👉ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የበጀት ዓመት ግምገማ። የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን እምቅ አቅሞችን በማልማት በሁሉም ዘርፎች የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መቻሉንና በቀጣይም አገራዊ ኢኒሼቲቮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። በተመሳሳይ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ በተፈጠረው "ንጋት ሐይቅ" ከተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ 10 ሺህ 799 ቶን ዓሳ ማምረት መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ኢትቻ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። 👉አፋር ክልል የገቢ አሰባሰብ ውጤት። በበጀት ዓመቱ ከ8 ቢሊዮን 524 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ አወል አብዱ ገልጸዋል። ለውጤቱ መገኘት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር መዘርጋቱ፣ የግብር ከፋዩ ግንዛቤ ማደግና የአመራሩ ቁርጠኝነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። 👉ሐረሪ ክልል የበጀት አፈጻጸምና የ2019 በጀት መጽደቅ። የ2018 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። ምክር ቤቱ የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት ለ2019 በጀት ዓመት 12 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በጀት አጽድቋል። ከበጀቱ ውስጥ ከፍተኛው ድርሻ ለካፒታል በጀት የተመደበ ሲሆን፣ ትኩረቱም ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ነው። 👉ኦሮሚያ ክልል የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሂደት። በ2018 በጀት ዓመት የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ የልማት ዕድሎችን፣ የሰው ኃይልንና ዕውቀትን አቀናጅቶ በመምራት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። በቀጣይም የተመዘገቡ ድሎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ከመደመር እሳቤ የተቀዱ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች በላቀ ቁርጠኝነትና በሕዝብ ተሳትፎ መመራት እንዳለባቸው የሥራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። 👉ደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ከ150 ሚሊዮን 250 ሺህ ብር በላይ ከምዝበራ ማዳንና በኦዲት ግኝት ማስመለስ መቻሉን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ አስታውቀዋል። ከዚህ ውስጥ 68.6 ሚሊዮን ብሩ በአስቸኳይ ሙስና መከላከል ሥራ ከምዝበራ የዳነ ነው። ከገንዘብ በተጨማሪ 14 ሺህ 673 ካሬ ሜትር የከተማ መሬት እና 645 ሄክታር የገጠር መሬት፣ እንዲሁም በርካታ የመንግሥትና የሕዝብ ሀብቶችን ማዳንና ማስመለስ ተችሏል። የአገልግሎት አፈጻጸሙን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል ቅንጅታዊ አሠራርን ማሳደግ እንደሚገባም ተገልጿል።
ትንታኔዎች
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 107
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 4358
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!  
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 3453
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 3406
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 10501
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 20737
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 13774
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 19528
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 101900
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 77000
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 56148
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 53701
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 38661
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 38292
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 37777
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 36686
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 101900
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 77000
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 56148
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 53701
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 6800
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 4663
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም