ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ማንችስተር ዩናይትድ ለአመታት ሲፈልገው የነበረውን ካርሎስ ባሌባን አስፈረመ
Aug 25, 2026 154
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ማንችስተር ዩናይትድ የካሜሮኑን አማካይ ካርሎስ ባሌባን ከብራይተን በ70 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረሙን ዛሬ አስታውቋል። የ22 ዓመቱ ተጫዋች በኦልድ ትራፎርድ ለቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራት የተፈራረመ ሲሆን፣ እስከ እ.አ.አ 2031 በሚቆየው በዚህ ውል ላይ የክለቡ ተጨማሪ የ12 ወራት የማራዘም አማራጭ ተካቷል። ባሌባ ወደ አዲሱ ክለቡ መቀላቀሉን አስመልክቶ በሰጠው አስተያየት፣ ለረጅም ጊዜ ለመቀላቀል ሳልመው በነበረው ማንችስተር ዩናይትድ መፈረም በመቻሌ ታላቅ ደስታና ክብር ይሰማኛል ብሏል። ከአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ጋር በመስራት እና የእሱን ልምድ በመጠቀም ብቃቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚፈልግም ገልጿል። ባሌባ በማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ስር በክረምቱ የዝውውር መስኮት የፈረመ ሶስተኛው የአማካይ ተጫዋች ሆኗል። ዩናይትድ ቀደም ሲል አንድሬ ሳንቶስን ከቼልሲ በ48 ሚሊዮን ፓውንድ እና ዩሪ ቲሊማንስን ከአስቶንቪላ በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረሙ ይታወቃል።
የመገጭ ግድብ የመደመር መንግስት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅም ማሳያ ነው
Aug 25, 2026 156
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦የመገጭ ግድብ የመደመር መንግስት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅም ማሳያ መሆኑን የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ገለጹ። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የመገጭ ግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ተቋማት ለተውጣጡ ጋዜጠኞች አስጎብኝቷል። የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፤የመገጭ ግድብ የጎንደር ከተማ የዘመናት ጥያቄ መሆኑን ገልጸዋል። የመገጭ ግድብ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለሕዝቡ ያልተሠራውን ተሠራ እየተባለ 18 ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰዋል። መገጭ ለንጹህ መጠጥ ውሃና ለመስኖ ልማት በመዋል ለኢትዮጵያ ብዙ ጥቅም ማስገኘት የሚችል ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ነገር ግን ፕሮጀክቱ በአግባቡ ባለመመራቱ፣ በጋ ላይ የተሠራው ክረምት ላይ በጎርፍ እየተናደ ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሕልውና ሥጋት፣ ለጣና ሐይቅ ደግሞ በደለል መሞላት ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ብለዋል። ይሁን እንጂ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ሰጭነት ፕሮጀክቱን እንደገና በማጥናት ሕዝብ ከባዶ ተስፋ ወደሚጨበጥ ሕልም ማምጣት እንደተቻለ ገልጸዋል። ይህም ለሕዝቡ ከሚሰጠው ቀጥተኛ ጥቅም ባለፈ፣ ዓባይ ወንዝና ጣና ሐይቅን ከደለል በመታደግ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት እንዳለው በተግባር ገልጧል ብለዋል። በመገጭ ግድብ ግንባታ የታየው ፈጣን የግንባታ ለውጥ የመደመር መንግሥት ፕሮጀክት ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅሙን በተግባር ያሳየበት መሆኑን ገልጸዋል። የመገጭ ግድብ ሰፊ የእርሻ መሬት ላለው የደንቢያ አካባቢ የልማት ተስፋ፤ ለጎንደር ከተማ ደግሞ የዘላቂ ንጹህ መጠጥ ውሃ ብስራት ይሆናል ብለዋል። ሕብረተሰቡ የግድቡን አስፈላጊነት በወጉ በመረዳት አካባቢውን በንቃት እየጠበቀ፣ የፕሮጀክቱን አፈጻጸም በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን ገልጸዋል። ለ18 ዓመታት ሕዝቡን በባዶ ተስፋና በጎርፍ ሲያማርር የነበረው የመገጭ ግድብ፣ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ በቅርቡ ይጠናቀቃል ብለዋል።  
ማዕከላቱ በሽታና ሙቀትን የሚቋቋሙ የስንዴ ዝርያዎችን በማውጣት የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደጉ ነው
Aug 25, 2026 144
አዳማ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፡-የግብርና የምርምር ማእከላት በቆላማ አካባቢዎች በሽታና ሙቀትን የሚቋቋሙ የስንዴ ዝርያዎችን በምርምር በማውጣት የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደጉ መሆናቸውን የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ። ብሔራዊ የዘር ብዜትና አጠቃቀም የአሰልጣኞች ሥልጠናና የባለድርሻ አካላት ምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ንጉሤ ደቻሳ እንዳሉት፤ የግብርና ምርምር ማዕከላት የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ፣ በማስተዋወቅ እንዲሁም ዘርን በማባዛት ለግብርና ምርትና ምርታማነት ማደግ ከፍተኛ ድርሻ እያበረከቱ ይገኛሉ። ለዚህም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በቆላማ አካባቢዎች በሽታና ሙቀትን የሚቋቋሙ የስንዴ ዝርያዎችን በምርምር በማፍለቅና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች በማቅረብ ረገድ ያደረጉት ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።   የስንዴ ሰብሎቹም በቆላማ አካባቢዎች በሽታንና ሙቀትን በመቋቋም የአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚነት ማሳደጋቸውን አስታውቀዋል። በዚህ ረገድ የአፍሪካ የግብርና ቴክኖሎጂ ማሸጋገሪያ ፕሮጀክት የመስኖ ስንዴ ቴክኖሎጂዎችን የማቅረብ እና መነሻ ዘሮችን የማባዛት ሥራን ሲደግፍ መቆየቱን ጠቁመዋል።   በኢንስቲትዩቱ የፕሮጀክቱ አስተባባሪና የቁሉምሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ዓለማየሁ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ በተደረገባቸው በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በአፋር ክልሎች የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ አዎንታዊ ውጤት ማስገኘቱን ተናግረዋል። በዚህም የአርሶ አደሩን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሻሻል አማካይ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በሄክታር 40 ኩንታል ማድረስ መቻሉንም አስረድተዋል።   ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደጀኔ ሂርጳ፤ ከግብርና ምርምር የሚወጡ የስንዴ ዝርያዎች በሽታን የመቋቋም አቅማቸውና ምርታማነታቸው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በፕሮጀክቱ ተሻሽለው የወጡ አዳዲስ ዝርያዎች በክልሉ በሄክታር የሚገኘውን ምርት 40 ኩንታል ማድረሳቸውንም አስረድተዋል።   ከፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች መካከል በአርሲ ዞን የሄጦሳ ወረዳ አርሶ አደር አበራ ደገፋ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የስንዴ ቴክኖሎጂን ተደራሽ በማድረጉ ምርታማነታቸውን በእጥፍ ማሳደግ እንደቻሉም ተናግረዋል።        
የአፍሪካን የጤና ሥርዓት ከጥገኝነት ለማላቀቅ ከቃል ኪዳን የተሻገረ ቁርጠኛ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ
Aug 25, 2026 226
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን የጤና ሥርዓት ከጥገኝነት ለማላቀቅ ከቃል ኪዳን የተሻገረ ቁርጠኛ የባለቤትነት እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ። በአምስት የጤና ዘርፍ ምሰሶዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ለአራት ቀናት የሚቆየው 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአድዋ ድል መታሰቢያ መካሄድ ጀምሯል።   የመድረኩ ዋና ዋና የጤና ምሰሶዎች ዘላቂ የጤና ፋይናንስና የዲጂታል ጤና ሥርዓት፣ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ እንዲሁም የጤና ባለሙያዎችና የሀገር ውስጥ ምርቶች አቅም ማሳደግ ናቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶች ምክንያት በዜጎች ጤና ስርዓት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ይገኛሉ። በዚህም አፍሪካ የዜጎቿን የጤና አጠባበቅ ስርዓት በማዘመን በተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ሁኔታ የሚደርስን የጤና ተጋላጭነት በራስ አቀም ምላሽ መስጠት እንዳለባት ተናግረዋል። እነዚህ ተግዳሮቶች አፍሪካ ቀጣናዊ ትብብር ውስጥ የጋራ ድምጿን ለማጠናከርና በጤና ጉዳዮቿ ላይ ሙሉ ባለቤትነትን ለመያዝ ታሪካዊ ዕድል እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል። አፍሪካ በግልጽና በደፋር አቅጣጫ የተመሠረተ የተቀናጀ የጋራ ስትራቴጂ እንደሚያስፈልጋት በመጠቆም፤ በጤና ላይ የምታደርገውን የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ማሳደግ እንዳለባትም አስታውቀዋል። የአህጉሪቷን የጤና ስርዓት ለማዘመንም ስትራቴጂክ አጋርነት በማጠናከር የጤና ደኅንነት የራስ መድኃኒቶች፣ ክትባቶችና የምርመራ መሣሪያዎች ማምረትን እንደሚጠይቅ ጠቁመዋል። በዓለም ጤና ድርጅትና በአፍሪካ የበሽታ ቁጥጥርና መከላከያ ማዕከል መካከል ተግባራዊ ቅንጅት በማጠናከር በጉባኤው የሚተላለፉ ውሳኔዎችን ከአጀንዳ 2063 ግብ ጋር አቆራኝቶ መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል።   ኢትዮጵያ ጤናን እንደ ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ኢንቨስትመንት በመቁጠር በራስ አቅም የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር አቅሟን ከጊዜ ወደጊዜ እያጎለበተች እንደሚገኝ ገልጸዋል። የጤና ሥርዓቱን ለማሻሻልና ለማስፋት የተከናወኑ ተግባራትም በእናቶች፣ ሕፃናትና ልጆች ላይ የሚከሰትን በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር አቅም ማጎልበቱን ተናግረዋል። የአፍሪካ ቀጣዩ የጤና ምዕራፍ ከጥገኝነት ይልቅ ባለቤትነትን፣ ከመበታተን ይልቅ ውህደትን፣ ከቃል ኪዳን ይልቅ ተግባራዊ እርምጃን የሚያስቀድም መሆን እንዳለበት አመላክተዋል። ኢትዮጵያ ቀጣናዊና አሕጉራዊ የጤና ኢንቨስትመንት አቅምን ለማጎልበት በሚደረገው ጥረት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ቁርጠኛ አቋም እንዳላት አረጋግጠዋል።  
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን መስራች ጋር ተወያዩ
Aug 25, 2026 190
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን መስራች ክሪስን በለነገዋ ጋር በቀጣይ በጋራ በሚሰሩባቸው ስራዎች ዙሪያ መወያየታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች እና የቦርድ ሃላፊ ክሪስ ሆን እና ቡድናቸውን ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከልን ማስጎብኘታቸውንም ገልጸዋል። ለነገዋ ጅማሮው በተለያዩ ማህበራዊ ችግር ውስጥ ያሉ ሴት እህቶቻችን ተስፋና እድላቸው እዲለመልም፣ ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ ከልብ በመነጨ ስሜት የተፀነሰ፣ ተፀንሶም ወደ ተግባር የተቀየረ ትልቅ ራዕይን የሰነቀ ስራ ነው ብለዋል።   የእነዚህ እህቶቻችንን ህይወት ለመቀየር፣ ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ከ2016 ዓ.ም ጀምረነው በ5 ዙር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች 3 ሺህ 259 ሰልጣኞችን በክህሎት እና በስብዕና ግንባታ አሰልጥነን ወደ ስራ አሰማርተናል ሲለም ገልጸዋል። ዛሬ ሁሉም ተመራቂዎች ክብር ያለው ኑሮ፣ ብሩህ ተስፋን ሰንቀው አዲስ ህይወት መኖር ጀምረዋል ብለዋል። “ከምንሰራቸው ስራዎች ሁሉ ትልቁ ስራ በሰው ላይ የምንሰራው፣ በተለይም በሴቶች ላይ የምንሰራው ነው” የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት የስራችን ማዕከል አድርገን እየፈፀምን እንገኛለን ነው ያሉት። በከተማችን ላይ ከሚታየው ለውጥ ሁሉ የሚልቀው በለነገዋ ሴቶች ላይ እያየን ያለው ለውጥ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ለ”ለነገዋ የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል” የሰነቅነው ራዕይ፣ በዓመት እስከ 10 ሺህ ሴቶችን የሚያበቃ፣ እንዲሁም አካታች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ልምድ የሚቀሰምበት የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ማስቻል መሆኑንም ጠቅሰዋል።   ይህ ራዕይ በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ሊደግፋን የመጡት የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች ክሪስን በለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል የምንሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች አስጎብኝተን በቀጣይም በጋራ በምንሰራቸው ስራዎች ዙሪያ ተወያይተናል ብለዋል።
የሚታይ
የመገጭ ግድብ የመደመር መንግስት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅም ማሳያ ነው
Aug 25, 2026 156
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦የመገጭ ግድብ የመደመር መንግስት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅም ማሳያ መሆኑን የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ገለጹ። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የመገጭ ግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ተቋማት ለተውጣጡ ጋዜጠኞች አስጎብኝቷል። የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፤የመገጭ ግድብ የጎንደር ከተማ የዘመናት ጥያቄ መሆኑን ገልጸዋል። የመገጭ ግድብ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለሕዝቡ ያልተሠራውን ተሠራ እየተባለ 18 ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰዋል። መገጭ ለንጹህ መጠጥ ውሃና ለመስኖ ልማት በመዋል ለኢትዮጵያ ብዙ ጥቅም ማስገኘት የሚችል ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ነገር ግን ፕሮጀክቱ በአግባቡ ባለመመራቱ፣ በጋ ላይ የተሠራው ክረምት ላይ በጎርፍ እየተናደ ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሕልውና ሥጋት፣ ለጣና ሐይቅ ደግሞ በደለል መሞላት ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ብለዋል። ይሁን እንጂ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ሰጭነት ፕሮጀክቱን እንደገና በማጥናት ሕዝብ ከባዶ ተስፋ ወደሚጨበጥ ሕልም ማምጣት እንደተቻለ ገልጸዋል። ይህም ለሕዝቡ ከሚሰጠው ቀጥተኛ ጥቅም ባለፈ፣ ዓባይ ወንዝና ጣና ሐይቅን ከደለል በመታደግ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት እንዳለው በተግባር ገልጧል ብለዋል። በመገጭ ግድብ ግንባታ የታየው ፈጣን የግንባታ ለውጥ የመደመር መንግሥት ፕሮጀክት ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅሙን በተግባር ያሳየበት መሆኑን ገልጸዋል። የመገጭ ግድብ ሰፊ የእርሻ መሬት ላለው የደንቢያ አካባቢ የልማት ተስፋ፤ ለጎንደር ከተማ ደግሞ የዘላቂ ንጹህ መጠጥ ውሃ ብስራት ይሆናል ብለዋል። ሕብረተሰቡ የግድቡን አስፈላጊነት በወጉ በመረዳት አካባቢውን በንቃት እየጠበቀ፣ የፕሮጀክቱን አፈጻጸም በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን ገልጸዋል። ለ18 ዓመታት ሕዝቡን በባዶ ተስፋና በጎርፍ ሲያማርር የነበረው የመገጭ ግድብ፣ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ በቅርቡ ይጠናቀቃል ብለዋል።  
የአፍሪካን የጤና ሥርዓት ከጥገኝነት ለማላቀቅ ከቃል ኪዳን የተሻገረ ቁርጠኛ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ
Aug 25, 2026 226
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን የጤና ሥርዓት ከጥገኝነት ለማላቀቅ ከቃል ኪዳን የተሻገረ ቁርጠኛ የባለቤትነት እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ። በአምስት የጤና ዘርፍ ምሰሶዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ለአራት ቀናት የሚቆየው 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአድዋ ድል መታሰቢያ መካሄድ ጀምሯል።   የመድረኩ ዋና ዋና የጤና ምሰሶዎች ዘላቂ የጤና ፋይናንስና የዲጂታል ጤና ሥርዓት፣ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ እንዲሁም የጤና ባለሙያዎችና የሀገር ውስጥ ምርቶች አቅም ማሳደግ ናቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶች ምክንያት በዜጎች ጤና ስርዓት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ይገኛሉ። በዚህም አፍሪካ የዜጎቿን የጤና አጠባበቅ ስርዓት በማዘመን በተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ሁኔታ የሚደርስን የጤና ተጋላጭነት በራስ አቀም ምላሽ መስጠት እንዳለባት ተናግረዋል። እነዚህ ተግዳሮቶች አፍሪካ ቀጣናዊ ትብብር ውስጥ የጋራ ድምጿን ለማጠናከርና በጤና ጉዳዮቿ ላይ ሙሉ ባለቤትነትን ለመያዝ ታሪካዊ ዕድል እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል። አፍሪካ በግልጽና በደፋር አቅጣጫ የተመሠረተ የተቀናጀ የጋራ ስትራቴጂ እንደሚያስፈልጋት በመጠቆም፤ በጤና ላይ የምታደርገውን የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ማሳደግ እንዳለባትም አስታውቀዋል። የአህጉሪቷን የጤና ስርዓት ለማዘመንም ስትራቴጂክ አጋርነት በማጠናከር የጤና ደኅንነት የራስ መድኃኒቶች፣ ክትባቶችና የምርመራ መሣሪያዎች ማምረትን እንደሚጠይቅ ጠቁመዋል። በዓለም ጤና ድርጅትና በአፍሪካ የበሽታ ቁጥጥርና መከላከያ ማዕከል መካከል ተግባራዊ ቅንጅት በማጠናከር በጉባኤው የሚተላለፉ ውሳኔዎችን ከአጀንዳ 2063 ግብ ጋር አቆራኝቶ መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል።   ኢትዮጵያ ጤናን እንደ ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ኢንቨስትመንት በመቁጠር በራስ አቅም የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር አቅሟን ከጊዜ ወደጊዜ እያጎለበተች እንደሚገኝ ገልጸዋል። የጤና ሥርዓቱን ለማሻሻልና ለማስፋት የተከናወኑ ተግባራትም በእናቶች፣ ሕፃናትና ልጆች ላይ የሚከሰትን በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር አቅም ማጎልበቱን ተናግረዋል። የአፍሪካ ቀጣዩ የጤና ምዕራፍ ከጥገኝነት ይልቅ ባለቤትነትን፣ ከመበታተን ይልቅ ውህደትን፣ ከቃል ኪዳን ይልቅ ተግባራዊ እርምጃን የሚያስቀድም መሆን እንዳለበት አመላክተዋል። ኢትዮጵያ ቀጣናዊና አሕጉራዊ የጤና ኢንቨስትመንት አቅምን ለማጎልበት በሚደረገው ጥረት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ቁርጠኛ አቋም እንዳላት አረጋግጠዋል።  
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን መስራች ጋር ተወያዩ
Aug 25, 2026 190
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን መስራች ክሪስን በለነገዋ ጋር በቀጣይ በጋራ በሚሰሩባቸው ስራዎች ዙሪያ መወያየታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች እና የቦርድ ሃላፊ ክሪስ ሆን እና ቡድናቸውን ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከልን ማስጎብኘታቸውንም ገልጸዋል። ለነገዋ ጅማሮው በተለያዩ ማህበራዊ ችግር ውስጥ ያሉ ሴት እህቶቻችን ተስፋና እድላቸው እዲለመልም፣ ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ ከልብ በመነጨ ስሜት የተፀነሰ፣ ተፀንሶም ወደ ተግባር የተቀየረ ትልቅ ራዕይን የሰነቀ ስራ ነው ብለዋል።   የእነዚህ እህቶቻችንን ህይወት ለመቀየር፣ ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ከ2016 ዓ.ም ጀምረነው በ5 ዙር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች 3 ሺህ 259 ሰልጣኞችን በክህሎት እና በስብዕና ግንባታ አሰልጥነን ወደ ስራ አሰማርተናል ሲለም ገልጸዋል። ዛሬ ሁሉም ተመራቂዎች ክብር ያለው ኑሮ፣ ብሩህ ተስፋን ሰንቀው አዲስ ህይወት መኖር ጀምረዋል ብለዋል። “ከምንሰራቸው ስራዎች ሁሉ ትልቁ ስራ በሰው ላይ የምንሰራው፣ በተለይም በሴቶች ላይ የምንሰራው ነው” የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት የስራችን ማዕከል አድርገን እየፈፀምን እንገኛለን ነው ያሉት። በከተማችን ላይ ከሚታየው ለውጥ ሁሉ የሚልቀው በለነገዋ ሴቶች ላይ እያየን ያለው ለውጥ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ለ”ለነገዋ የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል” የሰነቅነው ራዕይ፣ በዓመት እስከ 10 ሺህ ሴቶችን የሚያበቃ፣ እንዲሁም አካታች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ልምድ የሚቀሰምበት የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ማስቻል መሆኑንም ጠቅሰዋል።   ይህ ራዕይ በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ሊደግፋን የመጡት የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች ክሪስን በለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል የምንሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች አስጎብኝተን በቀጣይም በጋራ በምንሰራቸው ስራዎች ዙሪያ ተወያይተናል ብለዋል።
የአፍሪካ ሀገራት የጤና ተደራሽነትና ዘላቂነትን የሚያረጋግጡ አቅሞችን መገንባት ይጠበቅባቸዋል - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Aug 25, 2026 200
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ አባል ሀገራት የዜጎቻቸውን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ዘላቂነት የሚያረጋግጡ አቅሞችን መገንባት እንደሚጠበቅባቸው የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። በአምስት የጤና ዘርፍ ምሰሶዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ለአራት ቀናት የሚቆየው 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአድዋ ድል መታሰቢያ መካሄድ ጀምሯል።   የመድረኩ ዋና ዋና የጤና ምሰሶዎችም ዘላቂ የጤና ፋይናንስና የዲጂታል ጤና ሥርዓት፣ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ እንዲሁም የጤና ባለሙያዎችና የሀገር ውስጥ ምርቶች አቅም ማሳደግ ናቸው። በዚሁ ወቅት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ጨምሮ የአፍሪካ አባል ሀገራት መንግሥታት ከፍተኛ ሥራ ኃላፊዎች፣ የልማት አጋሮች እንዲሁም ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሥራ መሪዎች ታድመዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ አጋጣሚ እንዳሉት፤ ሁሉንም አማራጮች በመጠቀም የአህጉሪቱን የጤና ሉዓላዊነት ማረጋገጥ ቀጣይነት ያለው ተግባር ይጠይቃል። የአፍሪካን ጤና ሥርዓት ዘላቂነት በአስተማማኝ መሠረት ለመገንባት የፋይናንስ አቅምን በማጎልበት የምርምርና ፈጠራ አቅሞችን ማሳደግ እንደሚገባም አመላክተዋል።   የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ጭብጥ አፍሪካውያንን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማሻሻል በውሃና ንፅህና አጠባበቅ ላይ ትኩረት ማድረጉን ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትም የዜጎቻቸውን የጤና ሥርዓት የሚያሻሽሉ የፋይናንስ፣ የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በራስ አቅም ማቋቋም ባህል ማዳበር እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የአህጉሪቱን የጤና ሥርዓት ለማሻሻል ከአባል ሀገራት፣ የልማት አጋሮችና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም ከዓለም ጤና ድርጅትና ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር የአህጉሪቱን የጤና ሥርዓቶች በተቀናጀ ዕቅድ ለመምራት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በጉባኤው የሚደረጉ ውይይቶችና የሚወሰኑ ውሳኔዎች ለአፍሪካ የጤና ሉዓላዊነት፣ ራስን መቻልና ዘላቂ የጤና ሥርዓት ግንባታ ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ጠቁመዋል።
በአፍሪካ የጤና ሥርዓትን ለማዘመን የሀገራትን ስትራቴጂካዊ ትብብር ማጠናከር ወሳኝ ነው
Aug 25, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ የጤና ሥርዓትን ለማዘመን በሚደረገው ጥረት የሀገራትን ስትራቴጂካዊ ትብብር የበለጠ ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ። 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ኮሚቴ ጉባኤ በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶች ምክንያት በዜጎች ጤና ስርዓት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ይገኛሉ። በዚህም አፍሪካ የዜጎቿን የጤና አጠባበቅ ስርዓት በማዘመን በተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ሁኔታ የሚደርስን የጤና ተጋላጭነት በራስ አቅም ምላሽ መስጠት እንዳለባት ተናግረዋል። እነዚህ ተግዳሮቶች አፍሪካ ቀጣናዊ ትብብር ውስጥ የጋራ ድምጿን ለማጠናከርና በጤና ጉዳዮቿ ላይ ሙሉ ባለቤትነትን ለመያዝ ታሪካዊ ዕድል እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል። አፍሪካ በግልጽና በደፋር አቅጣጫ የተመሠረተ፣ የተቀናጀ የጋራ ስትራቴጂ እንደሚያስፈልጋት ጠቁመው፤ በጤና ላይ የምታደርገውን የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ማሳደግ እንዳለባትም አስታውቀዋል። የአህጉሪቷን የጤና ስርዓት ለማዘመንም ስትራቴጂክ አጋርነት በማጠናከር የጤና ደኅንነት የራስ መድኃኒቶች፣ ክትባቶችና የምርመራ መሣሪያዎችን ማምረትን እንደሚጠይቅ ጠቁመዋል። በዓለም ጤና ድርጅት እና በአፍሪካ የበሽታ ቁጥጥርና መከላከያ ማዕከል መካከል ተግባራዊ ቅንጅት ማጠናከር ይገባል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ በጉባኤው የሚተላለፉ ውሳኔዎችን ከአፍሪካ አጀንዳ 2063 ግብ ጋር አቆራኝቶ መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ጤናን እንደ ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ኢንቨስትመንት እንደምትመለከት ገልጸው፤ ለጤና የሚመደበው በጀት በተከታታይ እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል። በመሠረታዊ የጤና አገልግሎት ላይ የተደረገው ኢንቨስትመንት የጤና አገልግሎቶችን ወደ ማኅበረሰቡ ተደራሽ በማድረግ ሚሊዮኖችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል። በተጨማሪም የጤና ባለሙያዎችን ቁጥር በማሳደግ የጤና ሥርዓቱን ማጠናከሯን ጠቁመው፤ ይህም በእናቶች፣ ሕፃናት እና ልጆች የመኖር ዕድል ላይ ጉልህ መሻሻል እንዲመጣ ማድረጉን ጠቁመዋል። በአየር ንብረት ለውጥ የሚመጡ የጤና ስጋቶችን ለመቋቋምም ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብሯን በማስፋት ሚሊዮኖችን በማሳተፍ በርካታ ችግኞችን መትከሏን ተናግረዋል። በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የልማት ተግባራት ንጹሕ፣ ጤናማና ለነዋሪዎች የተሻለ የከተማ አካባቢን በመፍጠር የሕዝቡን ጤና እና የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። ዘላቂ የጤና ሥርዓት ያለ ሰላምና መረጋጋት ሊኖር እንደማይችል ገልጸው ባለፈው እሁድ ኢትዮጵያ ከተለያዩ የፖለቲካ አመለካከቶች የተውጣጡ ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች የተሳተፉበትን አካታች ብሔራዊ ምክክር በማካሄድ ትልቅ ምዕራፍ አሳልፋለች ብለዋል። ኢትዮጵያም በብሔራዊ ኢንቨስትመንት፣ በቀጣናዊ ትብብርና ለአህጉራዊ ተቋማት በማይናወጥ ድጋፍ የራሷን ድርሻ ለመወጣት ሙሉ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በክልሉ በፓርቲው መሪነት በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል
Aug 24, 2026 515
ሳውላ፤ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ። በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2018 በጀት አመት አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀምና የ2019 ዕቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሳውላ ከተማ እየተካሄደ ነው።   በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በፓርቲው መሪነት የተከናወኑ የልማት ኢንሼቲቮችና የንቅናቄ አጀንዳዎች የተሳኩና ውጤት የተገኘባቸው ናቸው። በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየውን ስኬት ለአብነት ጠቁመው በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብርም አበረታች ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል ። በተመሳሳይ በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የሀገር ውስጥ ምርትን በመተካት እንዲሁም ለወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ እመርታ መመዝገቡን አመልክተዋል ። በክልሉ ከተሞች የኮሪደር ልማት በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ በተመሳሳይ መልኩ የገጠሩን ሕብረተሰብ የኑሮ ዘይቤ በዘላቂነት ለመቀየር የተጀመረው ሞዴል የገጠር ኮሪደር ልማት ስራም ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል ። ባጠቃላይ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ባስገኛቸው ውጤቶች ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በማህበራዊ ልማት በኩል በትምህርትና በጤና ዘርፎች ጥራትን ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውንም አንስተዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለአረጋውያንና አቅም ለሌላቸው ወገኖች የተደረጉ የቤት አድሳትና የድጋፍ ስራዎች ኢትዮጵያዊ የመደጋገፍ ባህልን ያጎሉ፣ የእርሰ በርስ መስተጋብርን ያጠናከሩ ናቸዉ ብለዋል።   የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ በበኩላቸዉ በፓርቲዉ መሪነት በበጀት ዓመቱ በርካታ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። ይህም በዞኑ ዜጎችን በተለያየ መልኩ ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቁመው በህዝብ ተሳትፎ ውጤቱን ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል ። በመድረኩ በብልጽግና ፓርቲ የክልል፣ የዞኖችና የከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር ወደ መግባባት መሸጋገር የተቻለበት ነው – ተመካካሪዎች
Aug 24, 2026 455
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የልዩነት ምንጭ በነበሩ አጀንዳዎች ላይ በግልጽነት በመመካከር የጋራ መፍትሔ ሀሳቦች የተቀመጡበትና ወደ የጋራ መግባባት መምጣት የተቻለበት ወሳኝ መድረክ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋና ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የማጠቃለያ መርሐ ግብር ባለፈው ቅዳሜ ተከናውኗል። ከሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ማጠቃለያ በኋላ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች እንዳሉት፤ በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር ዘላቂ ልማትና ሰላምን ሊያረጋግጡ የሚችሉ ምክረ ሀሳቦችን በማፍለቅ ምክክራቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። ከሶማሌ ክልል የተወከሉት ተመካካሪ አብዱልቃድር መሐመድ እንዳሉት፤ ምክክሩ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ተመካካሪዎች በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንዲያነሱና እንዲመካከሩ ዕድል ፈጥሯል። መሰል የምክክር ሂደት በቀጣይም ሊገጥሙን ለሚችሉ ችግሮች መፍቻ ሊሆን ይገባል ብለዋል። በምክክር ሂደቱ የተለያዩ ሀሳቦች ቀርበው ልዩነቶችን በምክክር በማቀራረብ ወደ የጋራ መግባባት መምጣት ተችሏል ብለዋል።   ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብን በመወከል የተመካከሩት መቶ አለቃ ዘለቀ ጮቅሬ፤ ምክክሩ የሀገሪቱን ሰላምና አንድነት ዘላቂ በማድረግ ለሁለንተናዊ ዕድገት የሚያግዝ ሂደት እንደነበር ገልጸዋል። በምክክር ጉባኤው የልዩነት ምንጭ በነበሩ አጀንዳዎችና ኢትዮጵያ ወደፊት በሰላም እንዴት መቀጠል እንዳለባት በሰፊው መመካከራቸውንም አክለዋል። በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያን አሸናፊ ለማድረግና ሰላሟንና ልማቷን በዘላቂነት ማስቀጠል የሚያስችል ግልጽና አሳታፊ ምክክር አድርገናል ብለዋል።   ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕናን የወከሉት ተመካካሪ ጌታቸው ዮሐንስ በበኩላቸው፣ ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ የተስፋ ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ገልጸዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ሂደት ኢትዮጵያውያን ስለሀገራቸው የወደፊት አቅጣጫ በመመካከር፣ ችግሮቻቸውን ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ በማንሳት መፍትሔ የሚሆኑ ምክረ ሀሳቦችን ያቀረቡበት መሆኑን ጠቁመዋል። በምክክሩ የቀረቡ ምክረ ሀሳቦች ለቀጣይ ሀገራዊ ሥራዎች ጠቃሚ ግብዓት እንደሚሆኑ ጠቁመዋል። መንግሥትም ምክረ ሀሳቦቹን እንደግብዓት በመጠቀም የሕዝቦችን አንድነት የሚያጎለብቱና ለጋራ ራዕይ የሚያነሳሱ እርምጃዎችን እንዲወስድ የሚያስችሉ መሆናቸውን ተመካካሪው ገልጸዋል።  
የምክክር ጉባኤው የጋራ መግባባትን የሚያጎለብት ተስፋን የፈነጠቀ የወል ትርክት መገንቢያ ድልድይ ነው - የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
Aug 24, 2026 457
አዲስ አበባ፣ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የጋራ መግባባትን የሚያጎለብት ተስፋን የፈነጠቀ የወል ትርክት መገንቢያ ድልድይ መሆኑን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለአርባ ስድስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሂዷል። በነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የማጠቃለያ መርሐ ግብር በተካሄደለት የምክክር ጉባኤም በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ጉዳይ መክረዋል፤ ኢትዮጵያም አሸንፋለች። ይህም ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የዘለቁ የአለመግባባት ስብራቶችን በሐሳብ የበላይነት ላይ በተመሠረተ ጥበብ መፍትሔ መስጠት እንደሚችሉ ተስፋ የተጣለበት ውጤት አምጥተዋል። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው ሰላምና ልማትን የሚያሳልጥ የሐሳብ ድልድይ የተገነባበትና የጋራ መግባባት መንገድን፣ የመደማመጥና የጋራ ራዕይ መድረክ ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ወጣት ናታን ከፋለው፣ የምክክር ጉባኤው እኛ ኢትዮጵያውያን በራሳችን ጉዳዮች ላይ በመምከር የጋራ መፍትሔ መስጠት እንደምንችል በተግባር ያስመሰከረ ነው ብሏል። የጉባኤው ምክረ ሐሳቦችም በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የጸናች ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችሉ የጋራ የቃል ኪዳን ሰነድ መሆናቸውን ገልጿል። በተለይም አሰባሳቢና የወል ትርክት ግንባታን በመገንባት በሕዝብና በመንግሥት መካከል ጠንካራ የመተማመን ድልድይ ለመገንባት ዕድል የሚሰጥ ቁልፍ መሣሪያ መሆኑን ተናግሯል።   የልፍዋጋሽ ጫኔ በበኩላቸው፣ የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚያንጽ የወል ትርክትን መገንባት የሚያስችል የምክክር ባህል መሠረት የተጣለበት መሆኑን ገልጸዋል። በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ የወል ትርክት ግንባታም እንደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ያሉ ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ ወሳኝ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የፈለቁ ምክረ ሐሳቦችም በጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ላይ የተመሠረተ ልማትና ዕድገትን ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ተናግረዋል።   ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ፓስተር መርዕድ ኃይሌ በበኩላቸው፣ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የምክክር ምኅዳር ባለመፈጠሩ በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን መገንባት ሳይቻል ቆይቷል ብለዋል። በኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤም የዜጎችን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት የሚያስቀጥሉ ወሳኝ ምክረ ሐሳቦች የተንሸራሸሩበት መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤውም ዘላቂ ሰላምና ዕድገትን በማስፈን የተሻለች ኢትዮጵያን ለትውልድ ማሸጋገር የሚያስችል ዕድል ፈጥሮ ያለፈ የጋራ መግባቢያ ድልድይ መሆኑን ተናግረዋል።   ጉባኤው በዜጎች መካከል የቆዩ የአለመግባባት ችግሮችን የጋራ መፍትሔ ማበጀት የሚያስችሉ ምክረ ሐሳቦች የፈለቁበት ነው ያለችው ደግሞ ሌላኛዋ የመዲናዋ ነዋሪ ወጣት ቃልኪዳን አድማሱ ናት። የምክክር ጉባኤውም ለተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ ጠንካራ መሠረት ከመጣሉ ባሻገር ለወጣቶችና ለሁሉም ዜጎች የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው አመልክታለች።  
የጋራ ሀገራዊ ራዕይ ለመቅረፅ ትልቅ ምዕራፍ የከፈተው -የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ
Aug 24, 2026 434
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የልዩነት ምንጭ በነበሩ መሰረታዊ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር የወደፊት የጋራ ሀገራዊ ራዕይ ለመቅረጽ ትልቅ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለአርባ ስድስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሂዷል። በነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. የማጠቃለያ መርሐ ግብር በተካሄደለት የምክክር ጉባኤም፣ በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ጉዳይ መክረዋል፤ ኢትዮጵያም አሸንፋለች። ይህም ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የዘለቁ የአለመግባባት ስብራቶችን በሐሳብ የበላይነት ላይ በተመሠረተ ጥበብ መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ውጤት አምጥተዋል። በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተሳታፊዎች እንደገለጹት፣ የምክክር ጉባኤው በሀገሪቱ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ መሠረታዊ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የተመከረበት ነበር። በዚህም በሀገሪቱ ለረጅም ጊዜ የልዩነት ምንጭ ሆነው ለቆዩ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር፣ የጋራ የወደፊት ራዕይ ለመቅረጽ ትልቅ ምዕራፍ የከፈተና ለመጪው ትውልድ ጠንካራ መሠረት የተጣለበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነበር ብለዋል። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ታረቀኝ አብዱጀባር እንዳሉት፣ በሀገራችን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሁሉም ሰው የራሱን ብቻ ሳይሆን የሌሎችንም ጥያቄዎች ያዳመጠበትና የጋራ ምክረ ሐሳብ ያቀረበበት ጉባኤ እንደነበር ገልጸዋል። በዚህም ተመካካሪዎች በስምንቱም አጀንዳዎች ላይ በመመካከር፣ የጋራ ስምምነት ላይ በመድረስ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፍ አዲስ ተስፋና መሠረት መጣሉን ጠቁመዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ኤሊያስ ደባሱ በበኩላቸው፣ የምክክር ሂደቱ ከወረዳ ጀምሮ ሁሉንም አካላት ባካተተ መልኩ መካሄዱን ገልጸዋል። የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያ ማሸነፏ በተግባር የታየበትና ለአፍሪካ ተምሳሌት የሚሆን ስኬት መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያዊ መልክ ያለው ሐሳብ የተንጸባረቀበት ጉባኤ እንደነበር በመግለጽ፣ ይህ ምክክር ሀገራችንን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካም ትልቅ አርአያ የሚሆን ስኬት መሆኑን ተናግረዋል።   በተመሳሳይ ተመካካሪው አቶ ስዩም ዮሐንስ እንደገለጹት፣ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ በመመካከር ሀገርን የሚያሻግሩ ምክረ ሐሳቦች መቅረባቸውን አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላለፉት ዘመናት የልዩነት ምንጭ ለነበሩ ጉዳዮች የመፍትሔ ምክረ ሐሳቦችን ከማስቀመጥ ባለፈ፣ በቀጣይ ሊገጥሙ ለሚችሉ መሰል ጉዳዮች የመፍቻ ስልት የተቀየሰበት እንደነበርም ጠቅሰዋል። በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የጸደቁ ምክረ ሐሳቦች ወደ ተግባር ሲተረጎሙ፣ የምክክር ሂደቱ ውጤት ይበልጥ ተጨባጭ እንደሚሆን ገልጸዋል። እነዚህ የቀረቡ ምክረ ሐሳቦች ወደ ተግባር እንዲገቡ ማድረግም የሚቀጥለው ቁልፍ ሥራ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።  
በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር የማጽናት ትዕምርት
Aug 24, 2026 551
በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር የማጽናት ትዕምርት - የሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ገብሩ እና የኮማንዶ በረከት ምትኩ ታሪክ ሀገርን በማገልገል የማጽናት ጉዳይ በአንድ ትውልድ ተጀምሮ የሚጠናቀቅ አይደለም፤ በትውልድ ቅብብሎሽ ሂደት እየደረጀ የሚዘልቅ እንጂ። እሴት፣ አርበኝነት፣ ተግባራዊ ቁርጠኝነትና ስለሀገር የሚኖር የኃላፊነት ስሜት በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገርን በፍጹም ቁርጠኝነት ለማገልገል መነሳት፣ ሀገርን ለማጽናት ያለው ትርጉም የጎላ ነው። በዚህ ጽሑፍ ሀገርን በትውልድ ቅብብሎሽ የማጽናት ትክክለኛ ትዕምርት የሆነውን የአባትና ልጅ እውነተኛ ታሪክ እናካፍላችኋለን። አባት ሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ገብሩ፤ ልጅ ደግሞ ምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ ይባላሉ። ሁለቱም በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ውስጥ ሀገርን ለማጽናት በፍጹም ቁርጠኝነት በተመሳሳይ ሙያ ላይ ተሰማርተዋል። አባት የወታደርነት ሙያን በመቀላቀል የሌተናል ኮሎኔልነት ደረጃ ደርሰው ሀገራቸውን እያገለገሉበት ያለውን ዳና ልጃቸውም እንዲጋራው በማድረግ፣ አሁን ላይ በመከላከያ ሠራዊት የኮማንዶ ክፍልን መርጦ በመቀላቀል ሀገሩን እያገለገለ ይገኛል። አባት ሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ገብሩ በረዥም የአገልግሎት ዘመናቸው የተማሩትን የሀገር ፍቅር፣ ጽናትና ሀገራዊ ኃላፊነት ልጃቸውም በራሱ መንገድ በመቀበል ከቤተሰብ ታሪክ በላይ ሀገርን ለማጽናት የትውልድ ቅብብሎሽን ትርጉም በተግባር አሳይተዋል። በተለይም ልጃቸው ምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ የኮማንዶ ሥልጠና የሚጠይቀውን አካላዊ ዝግጁነት ሀገርን በቁርጠኝነት የማገልገል ተነሳሽነትና ጽናት፣ ትዕግሥትና ተልዕኮን በብቃትና በኃላፊነት የመወጣት መሻት የአባትና ልጅ ታሪክን ልዩ ያደርገዋል። ይህ የአባትና ልጅ ታሪክ ወታደርነት አንድ ሙያ ወይም የሥራ መደብ ብቻ ሳይሆን፣ ሀገርን በቁርጠኝነት፣ በጽናትና በታማኝነት ለማገልገል እንዲሁም የሀገርና የሕዝብን ደኅንነት በታማኝነት ለመጠበቅ የተገባ የባንዲራ ቃል ኪዳን ጥግ መሆኑን ያመላክታል። አባት የጀመረውን ሀገርን በቁርጠኝነት የማገልገል እውነተኛ መንገድ ልጅ መቀጠሉ፣ ሀገር ጸንታ የምትኖረው በትውልድ ቅብብሎሽ መሆኑን በተጨባጭ ያሳያል። አባት ሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ገብሩ፣ ልጃቸው ሙሉ ስብዕናን ተላብሶ እንዲያድግና ሀገሩን በፍጹም ታማኝነትና ቁርጠኝነት እንዲያገለግል የውትድርና ሙያን እንዲቀላቀል ፍላጎት እንደነበራቸው ገልጸዋል። በዚህም ልጃቸው ከነበረበት የደቡብ ዕዝ ወደ ልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል እንዲቀላቀል በማድረግ የኮማንዶ ሥልጠናን ተከታትሎ እንዲመረቅ በማድረጋቸው ልዩ ደስታ እንደፈጠረላቸውና ፍላጎታቸው መሳካቱን ጠቁመዋል። ልጃቸው ምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ፣ እንደ አባታቸው ወታደር በመሆን ሀገርን በታማኝነት ለማገልገል ትልቅ ሕልም እንደነበራቸውም ተናግረዋል። ፈታኝ ውስብስብና ሁለንተናዊ ዝግጁነትን የሚጠይቀውን የኮማንዶ ሥልጠና አጠናቀው ለስኬት እንዲበቁ፣ አባታቸው ሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ምክርና ጠንካራ ድጋፍ በመስጠት እንዳበረታቷቸው ገልጸዋል። የእኔ ሀገርን የማገልገል ዘመን እንዳያቆም፣ የአብራኬን ክፋይ ተክቼ ሀገር እንዲጠብቅ በመተካቴ ታላቅ ኩራት ይሰማኛል ነው ያሉት። ምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ በበኩሉ፤ የአባቱን የጀግንነት ገድልና ለሀገር ያላቸውን ጥልቅ ፍቅር በተግባር እያየ ማደጉን ተናግሯል። ከአባቱ የቀሰመውን ይህን ታላቅ ሀገርን በታማኝነት የማገልገል እሴት በመውረስ፣ በ2014 ዓ.ም የአባቱን ፈለግ በመከተል የመከላከያ ሠራዊቱን መቀላቀሉን ጠቁሟል። የውትድርና ሕይወት ከፍተኛ ጽናትና መስዋዕትነትን የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን ምክትል አሥር አለቃ በረከት ፈታኝ የሆነውን የኮማንዶ ሥልጠና በስኬት አጠናቆ ለምረቃና ሀገርን በቁርጠኝነት ለማገልገል መብቃቱን ገልጿል። በቀጣይም ከአባቴ በቀሰምኩት ጽናትና ወታደራዊ ሥነ-ምግባር፣ ሀገሬን በታማኝነትና በቁርጠኝነት ለማገልገል ዝግጁ ነኝ ብሏል። የምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ የአባቱን ፈለግ መከተል፣ ሀገርን በጀግኖች ትውልዶች ቅብብሎሽ በጽኑ መሠረት ላይ የማኖር ትልቅ ማሳያ ነው።  
ሀገራዊ ምክክሩ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር ሀገርን ለመገንባት አቅም የፈጠረ ነው
Aug 24, 2026 530
ጅግጅጋ፤ ነሀሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር ሀገርን ለመገንባት አቅም የፈጠረ መሆኑን የሶማሌ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። በሀገሪቱ የቆዩ ለአመግባባቶችን በምክክር ለመፍታት የተካሄደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በውጤት መጠናቀቁን የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሶማሌ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች እንዳሉት ሀገራዊ ምክክሩ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር ሀገርን ለመገንባት አቅም የፈጠረ ነው። ምክክሩ በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ የመወያየትና የመነጋገር ባህልን በማጎልበት በሀገሪቱ ዘላቂ ሠላምና እድገትን ለማምጣት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። ከሀገር ሽማግሌዎቹ መካከል ሱልጣን አብዲ ኡስማን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በጋራ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመምከር መፍትሔን ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በሀገሪቱ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር የተሻለች ሀገር ለመገንባት ትልቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። በምክክሩ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች መሳተፋቸውና በሰከነ መንገድ መካሄዱ ለቀጣይም ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን ጠቁመዋል። ሱልጣን አይደሩስ ጃማ በበኩላቸው ምክክሩ በሀገሪቱ ሠላምና ልማትን ለማስቀጠል የማይተካ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ የተለያዩ ሀሳቦችን በማሰባሰብ በሠለጠነ መንገድ በውይይት የመፍታት ባህልን ያዳበረ መሆኑን ተናግረዋል። ምክክሩ በሀገሪቱ እድገትን ለማፋጠን መሰረት በመጣል የዜጎች ተጠቃሚነት እንዲጎለብትና ለትውልድ ምቹ ሀገርን ለማውረስ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ሰው ለሀገር ግንባታ አሻራውን የሚያሳርፍበትን መደላድል የፈጠረ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሱልጣን አህመድ አቡበከር ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። ሱልጣን ዩሱፍ ሂስ ኑር በበኩላቸው ሀገራዊ ምክክሩ በጉዳዮች ላይ በጥልቀት በመወያየት መፍትሔን በማስቀመጥ በሀገሪቱ አዲስ የውይይት በር የከፈተ ነው ብለዋል። ይህም ምክክር ጉዳዮችን በሀይል ከማስፈጸም በመውጣት በሠለጠነ መንገድ በውይይት ለመፍታት የሚያስችል ባህልን ለማዳበር ልምድ የተወሰደበት ነው ብለዋል።
የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ዝግጁ ነን-ተመራቂ የጽናት ኮርስ ኮማንዶዎች
Aug 23, 2026 1263
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በአገኙት ስልጠና የሚሰጣቸውን ሀገራዊ ግዳጅ በውጤታማነት በመወጣት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆናቸውን ከልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል የተመረቁ የጽናት ኮርስ መሰረታዊ ኮማንዶዎች ገለጹ። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ለ45ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን "የጽናት ኮርስ መሠረታዊ ኮማንዶዎች" በትናንትናው ዕለት አስመርቋል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ባስተላለፉት መልእክት፤ የአየር ወለድና ኮማንዶ ኃይል በአካል ብቃቱ፣ በጽናቱና በከፍተኛ ወታደራዊ እውቀቱ የውጊያ አቅጣጫ ቀያሪ ኃይል መሆኑን ተናግረዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የጽናት ኮርስ መሠረታዊ ኮማንዶዎች ተመራቂ አባላት በበኩላቸው፤ በወሰዱት ስልጠና ከፍተኛ ወታደራዊ ልምድና ክህሎት መጨበጣቸውን ገልጸዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል መሠረታዊ ኮማንዶ አብዱልሰላም ስዩም ሀገር ያለ ሕዝብ፣ ሕዝብ ያለ ሀገር ተነጣጥለው ሊታዩ አይችሉም ብሏል። የሀገርና የሕዝብ ሉዓላዊነት ተጠብቆ እንዲቆይ ደግሞ ከወታደሩ ብዙ እንደሚጠበቅ ገልጾ፤ሀገርን በመውደድ በወታደርነት ማገልገል ክብር በመሆኑ ባገኘው ወታደራዊ ስልጠና ሀገሩን ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል።   ኢትዮጵያን በውትድርና ሙያ ለማገልገል በጽናት የወሰደችውን ስልጠና በማጠናቀቋ መደሰቷን የተናገረችው መሠረታዊ ኮማንዶ ፋንታዬ ያደታ በበኩሏ፤ በወሰደችው ወታደራዊ ስልጠና ኢትዮጵያ በምትፈልጋት ሀገራዊ ግዳጅ ሁሉ ኃላፊነቷን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።   ሌላኛው ተመራቂ መሠረታዊ ኮማንዶ ዳግም ዳዊት፤ በስልጠና ቆይታው ብቃት ያለው ወታደር መሆን የሚያስችለውን ትምህርትና ልምድ ማግኘቱን ተናግሯል። የስልጠና ሂደቱን በአግባቡ በማጠናቀቁ መደሰቱን ገልጾ፣በቀጣይም የሀገርን ሰላም ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።   መሠረታዊ ኮማንዶ ሙሉጌታ ግርማ ለውትድርና ያለው ልዩ ፍቅር ወደ ልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ገብቶ ስልጠናውን እንዲከታተል እንዳነሳሳው ገልጾ፤ በማዕከሉ ልዩ ልዩ ስልጠናዎችን መውሰዱንና በቀጣይም ባካበተው ወታደራዊ አቅም የሀገሩን ዳር ድንበር ለመጠበቅ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   መሠረታዊ ኮማንዶ ቃልኪዳን ጌታሁን በበኩሏ፤ በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል የወሰደችው ወታደራዊ ስልጠና ሀገሯን ለማገልገል ብቁ እና ዝግጁ እንዳደረጋት ገልጻ፣ ባካበተችው ወታደራዊ አቅም የሚሰጣትን ሀገራዊ ግዳጅ በውጤታማነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች።
ሕብረ ብሔራዊነት የተንጸባረቀበት የምክክር ጉባኤ
Aug 23, 2026 1184
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሕብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያዊነት የተንጸባረቀበት እና ኢትዮጵያን ወደ የተሻለ ደረጃ የሚያራምድ መድረክ መሆኑን በጉባኤው የተሳተፉ ተመካካሪዎች ገለጹ። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች እንደተናገሩት፤ ሀገራዊ ምክክሩ አሳታፊና አካታች የሆነ እንዲሁም ኢትዮጵያዊነት የተንጸባረቀበት መድረክ ነው። በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ተሳታፊ የነበሩት ተመካካሪ መሪማ ከማል እንደገለጹት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በስምንቱ አጀንዳዎች ላይ ጥልቅ ምክክር የተደረገበትና ሁላችንም ሀሳባችንን ያንጸባረቅንበት መድረክ ነበር።   ተመካካሪዎች ሀሳብና ጥያቄዎቻቸውን ያለተጽዕኖ በማቅረብ ምክክር የተደረገበትና ምክረ ሀሳቦች የቀረቡበት መድረክ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሌላኛው ተመካካሪ ተክለሃይማኖት ገብረእግዚ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያን ከአድዋ ድልና ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ ታሪክ የሰሩበት መድረክ ነበር ብለዋል። በእስካሁኑ የኢትዮጵያ ታሪክ የተስተዋለው የጠመንጃ ጉዞ አውዳሚ መሆኑን በመገንዘብ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር፣ ሌሎች ሀገራትም ችግራቸውን የፈቱበት መንገድ መሆኑን ተናግረዋል።   የምክክር ጉባኤው ሕብረ ብሔራዊነትና ኢትዮጵያዊነት የተንጸባረቀበት እና ኢትዮጵያን ወደተሻለ ደረጃ የሚያራምድ መሆኑንም ገልጸዋል።ምክክሩ እኔነትን ትተን ሀገር ወዳድነትን ያስቀደምንበት፣ እንዲሁም አጀንዳንና ሀገርን ማዕከል ያደረገ ምክክር ነው ብለዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ተቀራርበን በመመካከር ወደ መግባባት የመጣንበት ሂደት ነው" ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ ተመካካሪ ተስፋነሽ ኤርትሮ ናቸው።   የምክክር ጉባኤው ለትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን የምናስረክብበት ሂደት መሆኑንም አክለዋል።
ፖለቲካ
በክልሉ በፓርቲው መሪነት በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል
Aug 24, 2026 515
ሳውላ፤ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ። በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2018 በጀት አመት አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀምና የ2019 ዕቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሳውላ ከተማ እየተካሄደ ነው።   በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በፓርቲው መሪነት የተከናወኑ የልማት ኢንሼቲቮችና የንቅናቄ አጀንዳዎች የተሳኩና ውጤት የተገኘባቸው ናቸው። በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየውን ስኬት ለአብነት ጠቁመው በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብርም አበረታች ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል ። በተመሳሳይ በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የሀገር ውስጥ ምርትን በመተካት እንዲሁም ለወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ እመርታ መመዝገቡን አመልክተዋል ። በክልሉ ከተሞች የኮሪደር ልማት በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ በተመሳሳይ መልኩ የገጠሩን ሕብረተሰብ የኑሮ ዘይቤ በዘላቂነት ለመቀየር የተጀመረው ሞዴል የገጠር ኮሪደር ልማት ስራም ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል ። ባጠቃላይ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ባስገኛቸው ውጤቶች ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በማህበራዊ ልማት በኩል በትምህርትና በጤና ዘርፎች ጥራትን ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውንም አንስተዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለአረጋውያንና አቅም ለሌላቸው ወገኖች የተደረጉ የቤት አድሳትና የድጋፍ ስራዎች ኢትዮጵያዊ የመደጋገፍ ባህልን ያጎሉ፣ የእርሰ በርስ መስተጋብርን ያጠናከሩ ናቸዉ ብለዋል።   የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ በበኩላቸዉ በፓርቲዉ መሪነት በበጀት ዓመቱ በርካታ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። ይህም በዞኑ ዜጎችን በተለያየ መልኩ ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቁመው በህዝብ ተሳትፎ ውጤቱን ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል ። በመድረኩ በብልጽግና ፓርቲ የክልል፣ የዞኖችና የከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር ወደ መግባባት መሸጋገር የተቻለበት ነው – ተመካካሪዎች
Aug 24, 2026 455
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የልዩነት ምንጭ በነበሩ አጀንዳዎች ላይ በግልጽነት በመመካከር የጋራ መፍትሔ ሀሳቦች የተቀመጡበትና ወደ የጋራ መግባባት መምጣት የተቻለበት ወሳኝ መድረክ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋና ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የማጠቃለያ መርሐ ግብር ባለፈው ቅዳሜ ተከናውኗል። ከሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ማጠቃለያ በኋላ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች እንዳሉት፤ በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር ዘላቂ ልማትና ሰላምን ሊያረጋግጡ የሚችሉ ምክረ ሀሳቦችን በማፍለቅ ምክክራቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። ከሶማሌ ክልል የተወከሉት ተመካካሪ አብዱልቃድር መሐመድ እንዳሉት፤ ምክክሩ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ተመካካሪዎች በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንዲያነሱና እንዲመካከሩ ዕድል ፈጥሯል። መሰል የምክክር ሂደት በቀጣይም ሊገጥሙን ለሚችሉ ችግሮች መፍቻ ሊሆን ይገባል ብለዋል። በምክክር ሂደቱ የተለያዩ ሀሳቦች ቀርበው ልዩነቶችን በምክክር በማቀራረብ ወደ የጋራ መግባባት መምጣት ተችሏል ብለዋል።   ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብን በመወከል የተመካከሩት መቶ አለቃ ዘለቀ ጮቅሬ፤ ምክክሩ የሀገሪቱን ሰላምና አንድነት ዘላቂ በማድረግ ለሁለንተናዊ ዕድገት የሚያግዝ ሂደት እንደነበር ገልጸዋል። በምክክር ጉባኤው የልዩነት ምንጭ በነበሩ አጀንዳዎችና ኢትዮጵያ ወደፊት በሰላም እንዴት መቀጠል እንዳለባት በሰፊው መመካከራቸውንም አክለዋል። በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያን አሸናፊ ለማድረግና ሰላሟንና ልማቷን በዘላቂነት ማስቀጠል የሚያስችል ግልጽና አሳታፊ ምክክር አድርገናል ብለዋል።   ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕናን የወከሉት ተመካካሪ ጌታቸው ዮሐንስ በበኩላቸው፣ ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ የተስፋ ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ገልጸዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ሂደት ኢትዮጵያውያን ስለሀገራቸው የወደፊት አቅጣጫ በመመካከር፣ ችግሮቻቸውን ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ በማንሳት መፍትሔ የሚሆኑ ምክረ ሀሳቦችን ያቀረቡበት መሆኑን ጠቁመዋል። በምክክሩ የቀረቡ ምክረ ሀሳቦች ለቀጣይ ሀገራዊ ሥራዎች ጠቃሚ ግብዓት እንደሚሆኑ ጠቁመዋል። መንግሥትም ምክረ ሀሳቦቹን እንደግብዓት በመጠቀም የሕዝቦችን አንድነት የሚያጎለብቱና ለጋራ ራዕይ የሚያነሳሱ እርምጃዎችን እንዲወስድ የሚያስችሉ መሆናቸውን ተመካካሪው ገልጸዋል።  
የምክክር ጉባኤው የጋራ መግባባትን የሚያጎለብት ተስፋን የፈነጠቀ የወል ትርክት መገንቢያ ድልድይ ነው - የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
Aug 24, 2026 457
አዲስ አበባ፣ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የጋራ መግባባትን የሚያጎለብት ተስፋን የፈነጠቀ የወል ትርክት መገንቢያ ድልድይ መሆኑን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለአርባ ስድስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሂዷል። በነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የማጠቃለያ መርሐ ግብር በተካሄደለት የምክክር ጉባኤም በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ጉዳይ መክረዋል፤ ኢትዮጵያም አሸንፋለች። ይህም ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የዘለቁ የአለመግባባት ስብራቶችን በሐሳብ የበላይነት ላይ በተመሠረተ ጥበብ መፍትሔ መስጠት እንደሚችሉ ተስፋ የተጣለበት ውጤት አምጥተዋል። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው ሰላምና ልማትን የሚያሳልጥ የሐሳብ ድልድይ የተገነባበትና የጋራ መግባባት መንገድን፣ የመደማመጥና የጋራ ራዕይ መድረክ ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ወጣት ናታን ከፋለው፣ የምክክር ጉባኤው እኛ ኢትዮጵያውያን በራሳችን ጉዳዮች ላይ በመምከር የጋራ መፍትሔ መስጠት እንደምንችል በተግባር ያስመሰከረ ነው ብሏል። የጉባኤው ምክረ ሐሳቦችም በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የጸናች ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችሉ የጋራ የቃል ኪዳን ሰነድ መሆናቸውን ገልጿል። በተለይም አሰባሳቢና የወል ትርክት ግንባታን በመገንባት በሕዝብና በመንግሥት መካከል ጠንካራ የመተማመን ድልድይ ለመገንባት ዕድል የሚሰጥ ቁልፍ መሣሪያ መሆኑን ተናግሯል።   የልፍዋጋሽ ጫኔ በበኩላቸው፣ የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚያንጽ የወል ትርክትን መገንባት የሚያስችል የምክክር ባህል መሠረት የተጣለበት መሆኑን ገልጸዋል። በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ የወል ትርክት ግንባታም እንደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ያሉ ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ ወሳኝ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የፈለቁ ምክረ ሐሳቦችም በጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ላይ የተመሠረተ ልማትና ዕድገትን ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ተናግረዋል።   ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ፓስተር መርዕድ ኃይሌ በበኩላቸው፣ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የምክክር ምኅዳር ባለመፈጠሩ በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን መገንባት ሳይቻል ቆይቷል ብለዋል። በኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤም የዜጎችን ሕብረ ብሔራዊ አንድነት የሚያስቀጥሉ ወሳኝ ምክረ ሐሳቦች የተንሸራሸሩበት መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤውም ዘላቂ ሰላምና ዕድገትን በማስፈን የተሻለች ኢትዮጵያን ለትውልድ ማሸጋገር የሚያስችል ዕድል ፈጥሮ ያለፈ የጋራ መግባቢያ ድልድይ መሆኑን ተናግረዋል።   ጉባኤው በዜጎች መካከል የቆዩ የአለመግባባት ችግሮችን የጋራ መፍትሔ ማበጀት የሚያስችሉ ምክረ ሐሳቦች የፈለቁበት ነው ያለችው ደግሞ ሌላኛዋ የመዲናዋ ነዋሪ ወጣት ቃልኪዳን አድማሱ ናት። የምክክር ጉባኤውም ለተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ ጠንካራ መሠረት ከመጣሉ ባሻገር ለወጣቶችና ለሁሉም ዜጎች የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው አመልክታለች።  
የጋራ ሀገራዊ ራዕይ ለመቅረፅ ትልቅ ምዕራፍ የከፈተው -የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ
Aug 24, 2026 434
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የልዩነት ምንጭ በነበሩ መሰረታዊ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር የወደፊት የጋራ ሀገራዊ ራዕይ ለመቅረጽ ትልቅ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለአርባ ስድስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሂዷል። በነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. የማጠቃለያ መርሐ ግብር በተካሄደለት የምክክር ጉባኤም፣ በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ጉዳይ መክረዋል፤ ኢትዮጵያም አሸንፋለች። ይህም ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የዘለቁ የአለመግባባት ስብራቶችን በሐሳብ የበላይነት ላይ በተመሠረተ ጥበብ መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ውጤት አምጥተዋል። በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተሳታፊዎች እንደገለጹት፣ የምክክር ጉባኤው በሀገሪቱ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ መሠረታዊ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የተመከረበት ነበር። በዚህም በሀገሪቱ ለረጅም ጊዜ የልዩነት ምንጭ ሆነው ለቆዩ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር፣ የጋራ የወደፊት ራዕይ ለመቅረጽ ትልቅ ምዕራፍ የከፈተና ለመጪው ትውልድ ጠንካራ መሠረት የተጣለበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነበር ብለዋል። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ታረቀኝ አብዱጀባር እንዳሉት፣ በሀገራችን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሁሉም ሰው የራሱን ብቻ ሳይሆን የሌሎችንም ጥያቄዎች ያዳመጠበትና የጋራ ምክረ ሐሳብ ያቀረበበት ጉባኤ እንደነበር ገልጸዋል። በዚህም ተመካካሪዎች በስምንቱም አጀንዳዎች ላይ በመመካከር፣ የጋራ ስምምነት ላይ በመድረስ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፍ አዲስ ተስፋና መሠረት መጣሉን ጠቁመዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ኤሊያስ ደባሱ በበኩላቸው፣ የምክክር ሂደቱ ከወረዳ ጀምሮ ሁሉንም አካላት ባካተተ መልኩ መካሄዱን ገልጸዋል። የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያ ማሸነፏ በተግባር የታየበትና ለአፍሪካ ተምሳሌት የሚሆን ስኬት መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያዊ መልክ ያለው ሐሳብ የተንጸባረቀበት ጉባኤ እንደነበር በመግለጽ፣ ይህ ምክክር ሀገራችንን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካም ትልቅ አርአያ የሚሆን ስኬት መሆኑን ተናግረዋል።   በተመሳሳይ ተመካካሪው አቶ ስዩም ዮሐንስ እንደገለጹት፣ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ በመመካከር ሀገርን የሚያሻግሩ ምክረ ሐሳቦች መቅረባቸውን አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላለፉት ዘመናት የልዩነት ምንጭ ለነበሩ ጉዳዮች የመፍትሔ ምክረ ሐሳቦችን ከማስቀመጥ ባለፈ፣ በቀጣይ ሊገጥሙ ለሚችሉ መሰል ጉዳዮች የመፍቻ ስልት የተቀየሰበት እንደነበርም ጠቅሰዋል። በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የጸደቁ ምክረ ሐሳቦች ወደ ተግባር ሲተረጎሙ፣ የምክክር ሂደቱ ውጤት ይበልጥ ተጨባጭ እንደሚሆን ገልጸዋል። እነዚህ የቀረቡ ምክረ ሐሳቦች ወደ ተግባር እንዲገቡ ማድረግም የሚቀጥለው ቁልፍ ሥራ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።  
በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር የማጽናት ትዕምርት
Aug 24, 2026 551
በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር የማጽናት ትዕምርት - የሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ገብሩ እና የኮማንዶ በረከት ምትኩ ታሪክ ሀገርን በማገልገል የማጽናት ጉዳይ በአንድ ትውልድ ተጀምሮ የሚጠናቀቅ አይደለም፤ በትውልድ ቅብብሎሽ ሂደት እየደረጀ የሚዘልቅ እንጂ። እሴት፣ አርበኝነት፣ ተግባራዊ ቁርጠኝነትና ስለሀገር የሚኖር የኃላፊነት ስሜት በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገርን በፍጹም ቁርጠኝነት ለማገልገል መነሳት፣ ሀገርን ለማጽናት ያለው ትርጉም የጎላ ነው። በዚህ ጽሑፍ ሀገርን በትውልድ ቅብብሎሽ የማጽናት ትክክለኛ ትዕምርት የሆነውን የአባትና ልጅ እውነተኛ ታሪክ እናካፍላችኋለን። አባት ሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ገብሩ፤ ልጅ ደግሞ ምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ ይባላሉ። ሁለቱም በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ውስጥ ሀገርን ለማጽናት በፍጹም ቁርጠኝነት በተመሳሳይ ሙያ ላይ ተሰማርተዋል። አባት የወታደርነት ሙያን በመቀላቀል የሌተናል ኮሎኔልነት ደረጃ ደርሰው ሀገራቸውን እያገለገሉበት ያለውን ዳና ልጃቸውም እንዲጋራው በማድረግ፣ አሁን ላይ በመከላከያ ሠራዊት የኮማንዶ ክፍልን መርጦ በመቀላቀል ሀገሩን እያገለገለ ይገኛል። አባት ሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ገብሩ በረዥም የአገልግሎት ዘመናቸው የተማሩትን የሀገር ፍቅር፣ ጽናትና ሀገራዊ ኃላፊነት ልጃቸውም በራሱ መንገድ በመቀበል ከቤተሰብ ታሪክ በላይ ሀገርን ለማጽናት የትውልድ ቅብብሎሽን ትርጉም በተግባር አሳይተዋል። በተለይም ልጃቸው ምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ የኮማንዶ ሥልጠና የሚጠይቀውን አካላዊ ዝግጁነት ሀገርን በቁርጠኝነት የማገልገል ተነሳሽነትና ጽናት፣ ትዕግሥትና ተልዕኮን በብቃትና በኃላፊነት የመወጣት መሻት የአባትና ልጅ ታሪክን ልዩ ያደርገዋል። ይህ የአባትና ልጅ ታሪክ ወታደርነት አንድ ሙያ ወይም የሥራ መደብ ብቻ ሳይሆን፣ ሀገርን በቁርጠኝነት፣ በጽናትና በታማኝነት ለማገልገል እንዲሁም የሀገርና የሕዝብን ደኅንነት በታማኝነት ለመጠበቅ የተገባ የባንዲራ ቃል ኪዳን ጥግ መሆኑን ያመላክታል። አባት የጀመረውን ሀገርን በቁርጠኝነት የማገልገል እውነተኛ መንገድ ልጅ መቀጠሉ፣ ሀገር ጸንታ የምትኖረው በትውልድ ቅብብሎሽ መሆኑን በተጨባጭ ያሳያል። አባት ሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ገብሩ፣ ልጃቸው ሙሉ ስብዕናን ተላብሶ እንዲያድግና ሀገሩን በፍጹም ታማኝነትና ቁርጠኝነት እንዲያገለግል የውትድርና ሙያን እንዲቀላቀል ፍላጎት እንደነበራቸው ገልጸዋል። በዚህም ልጃቸው ከነበረበት የደቡብ ዕዝ ወደ ልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል እንዲቀላቀል በማድረግ የኮማንዶ ሥልጠናን ተከታትሎ እንዲመረቅ በማድረጋቸው ልዩ ደስታ እንደፈጠረላቸውና ፍላጎታቸው መሳካቱን ጠቁመዋል። ልጃቸው ምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ፣ እንደ አባታቸው ወታደር በመሆን ሀገርን በታማኝነት ለማገልገል ትልቅ ሕልም እንደነበራቸውም ተናግረዋል። ፈታኝ ውስብስብና ሁለንተናዊ ዝግጁነትን የሚጠይቀውን የኮማንዶ ሥልጠና አጠናቀው ለስኬት እንዲበቁ፣ አባታቸው ሌተናል ኮሎኔል ምትኩ ምክርና ጠንካራ ድጋፍ በመስጠት እንዳበረታቷቸው ገልጸዋል። የእኔ ሀገርን የማገልገል ዘመን እንዳያቆም፣ የአብራኬን ክፋይ ተክቼ ሀገር እንዲጠብቅ በመተካቴ ታላቅ ኩራት ይሰማኛል ነው ያሉት። ምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ በበኩሉ፤ የአባቱን የጀግንነት ገድልና ለሀገር ያላቸውን ጥልቅ ፍቅር በተግባር እያየ ማደጉን ተናግሯል። ከአባቱ የቀሰመውን ይህን ታላቅ ሀገርን በታማኝነት የማገልገል እሴት በመውረስ፣ በ2014 ዓ.ም የአባቱን ፈለግ በመከተል የመከላከያ ሠራዊቱን መቀላቀሉን ጠቁሟል። የውትድርና ሕይወት ከፍተኛ ጽናትና መስዋዕትነትን የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን ምክትል አሥር አለቃ በረከት ፈታኝ የሆነውን የኮማንዶ ሥልጠና በስኬት አጠናቆ ለምረቃና ሀገርን በቁርጠኝነት ለማገልገል መብቃቱን ገልጿል። በቀጣይም ከአባቴ በቀሰምኩት ጽናትና ወታደራዊ ሥነ-ምግባር፣ ሀገሬን በታማኝነትና በቁርጠኝነት ለማገልገል ዝግጁ ነኝ ብሏል። የምክትል አሥር አለቃ በረከት ምትኩ የአባቱን ፈለግ መከተል፣ ሀገርን በጀግኖች ትውልዶች ቅብብሎሽ በጽኑ መሠረት ላይ የማኖር ትልቅ ማሳያ ነው።  
ሀገራዊ ምክክሩ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር ሀገርን ለመገንባት አቅም የፈጠረ ነው
Aug 24, 2026 530
ጅግጅጋ፤ ነሀሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር ሀገርን ለመገንባት አቅም የፈጠረ መሆኑን የሶማሌ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ። በሀገሪቱ የቆዩ ለአመግባባቶችን በምክክር ለመፍታት የተካሄደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በውጤት መጠናቀቁን የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሶማሌ ክልል የሀገር ሽማግሌዎች እንዳሉት ሀገራዊ ምክክሩ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር ሀገርን ለመገንባት አቅም የፈጠረ ነው። ምክክሩ በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ የመወያየትና የመነጋገር ባህልን በማጎልበት በሀገሪቱ ዘላቂ ሠላምና እድገትን ለማምጣት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። ከሀገር ሽማግሌዎቹ መካከል ሱልጣን አብዲ ኡስማን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በጋራ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመምከር መፍትሔን ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በሀገሪቱ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር የተሻለች ሀገር ለመገንባት ትልቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። በምክክሩ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች መሳተፋቸውና በሰከነ መንገድ መካሄዱ ለቀጣይም ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን ጠቁመዋል። ሱልጣን አይደሩስ ጃማ በበኩላቸው ምክክሩ በሀገሪቱ ሠላምና ልማትን ለማስቀጠል የማይተካ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ የተለያዩ ሀሳቦችን በማሰባሰብ በሠለጠነ መንገድ በውይይት የመፍታት ባህልን ያዳበረ መሆኑን ተናግረዋል። ምክክሩ በሀገሪቱ እድገትን ለማፋጠን መሰረት በመጣል የዜጎች ተጠቃሚነት እንዲጎለብትና ለትውልድ ምቹ ሀገርን ለማውረስ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ሰው ለሀገር ግንባታ አሻራውን የሚያሳርፍበትን መደላድል የፈጠረ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሱልጣን አህመድ አቡበከር ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። ሱልጣን ዩሱፍ ሂስ ኑር በበኩላቸው ሀገራዊ ምክክሩ በጉዳዮች ላይ በጥልቀት በመወያየት መፍትሔን በማስቀመጥ በሀገሪቱ አዲስ የውይይት በር የከፈተ ነው ብለዋል። ይህም ምክክር ጉዳዮችን በሀይል ከማስፈጸም በመውጣት በሠለጠነ መንገድ በውይይት ለመፍታት የሚያስችል ባህልን ለማዳበር ልምድ የተወሰደበት ነው ብለዋል።
የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ዝግጁ ነን-ተመራቂ የጽናት ኮርስ ኮማንዶዎች
Aug 23, 2026 1263
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በአገኙት ስልጠና የሚሰጣቸውን ሀገራዊ ግዳጅ በውጤታማነት በመወጣት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆናቸውን ከልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል የተመረቁ የጽናት ኮርስ መሰረታዊ ኮማንዶዎች ገለጹ። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ለ45ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን "የጽናት ኮርስ መሠረታዊ ኮማንዶዎች" በትናንትናው ዕለት አስመርቋል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ባስተላለፉት መልእክት፤ የአየር ወለድና ኮማንዶ ኃይል በአካል ብቃቱ፣ በጽናቱና በከፍተኛ ወታደራዊ እውቀቱ የውጊያ አቅጣጫ ቀያሪ ኃይል መሆኑን ተናግረዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የጽናት ኮርስ መሠረታዊ ኮማንዶዎች ተመራቂ አባላት በበኩላቸው፤ በወሰዱት ስልጠና ከፍተኛ ወታደራዊ ልምድና ክህሎት መጨበጣቸውን ገልጸዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል መሠረታዊ ኮማንዶ አብዱልሰላም ስዩም ሀገር ያለ ሕዝብ፣ ሕዝብ ያለ ሀገር ተነጣጥለው ሊታዩ አይችሉም ብሏል። የሀገርና የሕዝብ ሉዓላዊነት ተጠብቆ እንዲቆይ ደግሞ ከወታደሩ ብዙ እንደሚጠበቅ ገልጾ፤ሀገርን በመውደድ በወታደርነት ማገልገል ክብር በመሆኑ ባገኘው ወታደራዊ ስልጠና ሀገሩን ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል።   ኢትዮጵያን በውትድርና ሙያ ለማገልገል በጽናት የወሰደችውን ስልጠና በማጠናቀቋ መደሰቷን የተናገረችው መሠረታዊ ኮማንዶ ፋንታዬ ያደታ በበኩሏ፤ በወሰደችው ወታደራዊ ስልጠና ኢትዮጵያ በምትፈልጋት ሀገራዊ ግዳጅ ሁሉ ኃላፊነቷን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።   ሌላኛው ተመራቂ መሠረታዊ ኮማንዶ ዳግም ዳዊት፤ በስልጠና ቆይታው ብቃት ያለው ወታደር መሆን የሚያስችለውን ትምህርትና ልምድ ማግኘቱን ተናግሯል። የስልጠና ሂደቱን በአግባቡ በማጠናቀቁ መደሰቱን ገልጾ፣በቀጣይም የሀገርን ሰላም ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።   መሠረታዊ ኮማንዶ ሙሉጌታ ግርማ ለውትድርና ያለው ልዩ ፍቅር ወደ ልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ገብቶ ስልጠናውን እንዲከታተል እንዳነሳሳው ገልጾ፤ በማዕከሉ ልዩ ልዩ ስልጠናዎችን መውሰዱንና በቀጣይም ባካበተው ወታደራዊ አቅም የሀገሩን ዳር ድንበር ለመጠበቅ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   መሠረታዊ ኮማንዶ ቃልኪዳን ጌታሁን በበኩሏ፤ በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል የወሰደችው ወታደራዊ ስልጠና ሀገሯን ለማገልገል ብቁ እና ዝግጁ እንዳደረጋት ገልጻ፣ ባካበተችው ወታደራዊ አቅም የሚሰጣትን ሀገራዊ ግዳጅ በውጤታማነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች።
ሕብረ ብሔራዊነት የተንጸባረቀበት የምክክር ጉባኤ
Aug 23, 2026 1184
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሕብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያዊነት የተንጸባረቀበት እና ኢትዮጵያን ወደ የተሻለ ደረጃ የሚያራምድ መድረክ መሆኑን በጉባኤው የተሳተፉ ተመካካሪዎች ገለጹ። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች እንደተናገሩት፤ ሀገራዊ ምክክሩ አሳታፊና አካታች የሆነ እንዲሁም ኢትዮጵያዊነት የተንጸባረቀበት መድረክ ነው። በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ተሳታፊ የነበሩት ተመካካሪ መሪማ ከማል እንደገለጹት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በስምንቱ አጀንዳዎች ላይ ጥልቅ ምክክር የተደረገበትና ሁላችንም ሀሳባችንን ያንጸባረቅንበት መድረክ ነበር።   ተመካካሪዎች ሀሳብና ጥያቄዎቻቸውን ያለተጽዕኖ በማቅረብ ምክክር የተደረገበትና ምክረ ሀሳቦች የቀረቡበት መድረክ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሌላኛው ተመካካሪ ተክለሃይማኖት ገብረእግዚ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያን ከአድዋ ድልና ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ ታሪክ የሰሩበት መድረክ ነበር ብለዋል። በእስካሁኑ የኢትዮጵያ ታሪክ የተስተዋለው የጠመንጃ ጉዞ አውዳሚ መሆኑን በመገንዘብ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር፣ ሌሎች ሀገራትም ችግራቸውን የፈቱበት መንገድ መሆኑን ተናግረዋል።   የምክክር ጉባኤው ሕብረ ብሔራዊነትና ኢትዮጵያዊነት የተንጸባረቀበት እና ኢትዮጵያን ወደተሻለ ደረጃ የሚያራምድ መሆኑንም ገልጸዋል።ምክክሩ እኔነትን ትተን ሀገር ወዳድነትን ያስቀደምንበት፣ እንዲሁም አጀንዳንና ሀገርን ማዕከል ያደረገ ምክክር ነው ብለዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ተቀራርበን በመመካከር ወደ መግባባት የመጣንበት ሂደት ነው" ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ ተመካካሪ ተስፋነሽ ኤርትሮ ናቸው።   የምክክር ጉባኤው ለትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን የምናስረክብበት ሂደት መሆኑንም አክለዋል።
ማህበራዊ
የአፍሪካን የጤና ሥርዓት ከጥገኝነት ለማላቀቅ ከቃል ኪዳን የተሻገረ ቁርጠኛ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ
Aug 25, 2026 226
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን የጤና ሥርዓት ከጥገኝነት ለማላቀቅ ከቃል ኪዳን የተሻገረ ቁርጠኛ የባለቤትነት እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ። በአምስት የጤና ዘርፍ ምሰሶዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ለአራት ቀናት የሚቆየው 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአድዋ ድል መታሰቢያ መካሄድ ጀምሯል።   የመድረኩ ዋና ዋና የጤና ምሰሶዎች ዘላቂ የጤና ፋይናንስና የዲጂታል ጤና ሥርዓት፣ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ እንዲሁም የጤና ባለሙያዎችና የሀገር ውስጥ ምርቶች አቅም ማሳደግ ናቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶች ምክንያት በዜጎች ጤና ስርዓት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ይገኛሉ። በዚህም አፍሪካ የዜጎቿን የጤና አጠባበቅ ስርዓት በማዘመን በተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ሁኔታ የሚደርስን የጤና ተጋላጭነት በራስ አቀም ምላሽ መስጠት እንዳለባት ተናግረዋል። እነዚህ ተግዳሮቶች አፍሪካ ቀጣናዊ ትብብር ውስጥ የጋራ ድምጿን ለማጠናከርና በጤና ጉዳዮቿ ላይ ሙሉ ባለቤትነትን ለመያዝ ታሪካዊ ዕድል እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል። አፍሪካ በግልጽና በደፋር አቅጣጫ የተመሠረተ የተቀናጀ የጋራ ስትራቴጂ እንደሚያስፈልጋት በመጠቆም፤ በጤና ላይ የምታደርገውን የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ማሳደግ እንዳለባትም አስታውቀዋል። የአህጉሪቷን የጤና ስርዓት ለማዘመንም ስትራቴጂክ አጋርነት በማጠናከር የጤና ደኅንነት የራስ መድኃኒቶች፣ ክትባቶችና የምርመራ መሣሪያዎች ማምረትን እንደሚጠይቅ ጠቁመዋል። በዓለም ጤና ድርጅትና በአፍሪካ የበሽታ ቁጥጥርና መከላከያ ማዕከል መካከል ተግባራዊ ቅንጅት በማጠናከር በጉባኤው የሚተላለፉ ውሳኔዎችን ከአጀንዳ 2063 ግብ ጋር አቆራኝቶ መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል።   ኢትዮጵያ ጤናን እንደ ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ኢንቨስትመንት በመቁጠር በራስ አቅም የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር አቅሟን ከጊዜ ወደጊዜ እያጎለበተች እንደሚገኝ ገልጸዋል። የጤና ሥርዓቱን ለማሻሻልና ለማስፋት የተከናወኑ ተግባራትም በእናቶች፣ ሕፃናትና ልጆች ላይ የሚከሰትን በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር አቅም ማጎልበቱን ተናግረዋል። የአፍሪካ ቀጣዩ የጤና ምዕራፍ ከጥገኝነት ይልቅ ባለቤትነትን፣ ከመበታተን ይልቅ ውህደትን፣ ከቃል ኪዳን ይልቅ ተግባራዊ እርምጃን የሚያስቀድም መሆን እንዳለበት አመላክተዋል። ኢትዮጵያ ቀጣናዊና አሕጉራዊ የጤና ኢንቨስትመንት አቅምን ለማጎልበት በሚደረገው ጥረት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ቁርጠኛ አቋም እንዳላት አረጋግጠዋል።  
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን መስራች ጋር ተወያዩ
Aug 25, 2026 190
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን መስራች ክሪስን በለነገዋ ጋር በቀጣይ በጋራ በሚሰሩባቸው ስራዎች ዙሪያ መወያየታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች እና የቦርድ ሃላፊ ክሪስ ሆን እና ቡድናቸውን ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከልን ማስጎብኘታቸውንም ገልጸዋል። ለነገዋ ጅማሮው በተለያዩ ማህበራዊ ችግር ውስጥ ያሉ ሴት እህቶቻችን ተስፋና እድላቸው እዲለመልም፣ ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ ከልብ በመነጨ ስሜት የተፀነሰ፣ ተፀንሶም ወደ ተግባር የተቀየረ ትልቅ ራዕይን የሰነቀ ስራ ነው ብለዋል።   የእነዚህ እህቶቻችንን ህይወት ለመቀየር፣ ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ከ2016 ዓ.ም ጀምረነው በ5 ዙር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች 3 ሺህ 259 ሰልጣኞችን በክህሎት እና በስብዕና ግንባታ አሰልጥነን ወደ ስራ አሰማርተናል ሲለም ገልጸዋል። ዛሬ ሁሉም ተመራቂዎች ክብር ያለው ኑሮ፣ ብሩህ ተስፋን ሰንቀው አዲስ ህይወት መኖር ጀምረዋል ብለዋል። “ከምንሰራቸው ስራዎች ሁሉ ትልቁ ስራ በሰው ላይ የምንሰራው፣ በተለይም በሴቶች ላይ የምንሰራው ነው” የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት የስራችን ማዕከል አድርገን እየፈፀምን እንገኛለን ነው ያሉት። በከተማችን ላይ ከሚታየው ለውጥ ሁሉ የሚልቀው በለነገዋ ሴቶች ላይ እያየን ያለው ለውጥ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ለ”ለነገዋ የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል” የሰነቅነው ራዕይ፣ በዓመት እስከ 10 ሺህ ሴቶችን የሚያበቃ፣ እንዲሁም አካታች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ልምድ የሚቀሰምበት የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ማስቻል መሆኑንም ጠቅሰዋል።   ይህ ራዕይ በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ሊደግፋን የመጡት የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች ክሪስን በለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል የምንሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች አስጎብኝተን በቀጣይም በጋራ በምንሰራቸው ስራዎች ዙሪያ ተወያይተናል ብለዋል።
የአፍሪካ ሀገራት የጤና ተደራሽነትና ዘላቂነትን የሚያረጋግጡ አቅሞችን መገንባት ይጠበቅባቸዋል - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Aug 25, 2026 200
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ አባል ሀገራት የዜጎቻቸውን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትና ዘላቂነት የሚያረጋግጡ አቅሞችን መገንባት እንደሚጠበቅባቸው የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። በአምስት የጤና ዘርፍ ምሰሶዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ለአራት ቀናት የሚቆየው 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአድዋ ድል መታሰቢያ መካሄድ ጀምሯል።   የመድረኩ ዋና ዋና የጤና ምሰሶዎችም ዘላቂ የጤና ፋይናንስና የዲጂታል ጤና ሥርዓት፣ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ እንዲሁም የጤና ባለሙያዎችና የሀገር ውስጥ ምርቶች አቅም ማሳደግ ናቸው። በዚሁ ወቅት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ጨምሮ የአፍሪካ አባል ሀገራት መንግሥታት ከፍተኛ ሥራ ኃላፊዎች፣ የልማት አጋሮች እንዲሁም ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሥራ መሪዎች ታድመዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ አጋጣሚ እንዳሉት፤ ሁሉንም አማራጮች በመጠቀም የአህጉሪቱን የጤና ሉዓላዊነት ማረጋገጥ ቀጣይነት ያለው ተግባር ይጠይቃል። የአፍሪካን ጤና ሥርዓት ዘላቂነት በአስተማማኝ መሠረት ለመገንባት የፋይናንስ አቅምን በማጎልበት የምርምርና ፈጠራ አቅሞችን ማሳደግ እንደሚገባም አመላክተዋል።   የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ጭብጥ አፍሪካውያንን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማሻሻል በውሃና ንፅህና አጠባበቅ ላይ ትኩረት ማድረጉን ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትም የዜጎቻቸውን የጤና ሥርዓት የሚያሻሽሉ የፋይናንስ፣ የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በራስ አቅም ማቋቋም ባህል ማዳበር እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የአህጉሪቱን የጤና ሥርዓት ለማሻሻል ከአባል ሀገራት፣ የልማት አጋሮችና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም ከዓለም ጤና ድርጅትና ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር የአህጉሪቱን የጤና ሥርዓቶች በተቀናጀ ዕቅድ ለመምራት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በጉባኤው የሚደረጉ ውይይቶችና የሚወሰኑ ውሳኔዎች ለአፍሪካ የጤና ሉዓላዊነት፣ ራስን መቻልና ዘላቂ የጤና ሥርዓት ግንባታ ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ጠቁመዋል።
በዞኑ የትምህርት ጥራትንና ተሳትፎን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል
Aug 25, 2026 118
ገንዳ ውኃ፣ ነሐሴ19/2018 (ኢዜአ):- በምዕራብ ጎንደር ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የትምህርት ጥራትንና ተሳትፎን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። የዞኑ ትምህርት መምሪያ በበኩሉ በትምህርት ዘመኑ ከ152 ሺህ በላይ ተማሪዎችን መዝግቦ ለማስተማር ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል። በዞኑ የተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪ ምዝገባ ንቅናቄ መድረክ በዛሬው ዕለት በገንዳ ውኃ ከተማ ተካሄዷል።   የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የትምህርት ጥራትንና ተሳትፎን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል። የተገኙ ተሞክሮዎችን በመቀመርና ችግሮችን በማረም በአዲሱ የትምህርት ዘመን የሚመዘገቡ ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ መዝግቦ ለማስተማር ዝግጅት መደረጉንም ገልጸዋል። በዞን፣ በወረዳና በከተማ አስተዳደር ደረጃ ያለው አመራርም ለትምህርት ምዝገባ ሥራው ልዩ ትኩረት በመስጠት የተያዘውን ግብ ለማሳካት መረባረብ እንዳለበትም አሳስበዋል። የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ አያና በበኩላቸው፤ በዞኑ በአዲሱ የትምህርት ዘመን ከ152 ሺህ በላይ ተማሪዎችን መዝግቦ ለማስተማር ወደ ሥራ ተገብቷል ብለዋል። በተጀመረው የሙከራ ምዝገባ በሰባት ቅድመ-አንደኛ ደረጃ እና በዘጠኝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ዕቅዱን 100 በመቶ ማሳካት መቻሉን አስረድተዋል። ይህም ተማሪዎችን በወቅቱ ትምህርት በማስጀመር የትምህርት ተደራሽነትን፣ ጥራትንና አግባብነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። በክረምት ወራቱም የትምህርት ቤቶች ጥገናን፣ መሠረተ ልማትን ማሟላትና ውብና ማራኪ ማድረግን የመሳሰሉ ተግባራትን በማከናወን የተሳካ የትምህርት አጀማመር እንዲኖር እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል። የቀጣይ ትውልድ ግንባታ መሠረት የሆነውን ትምህርት ለማጠናከር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንዳለ ማሩ ናቸው። በዚህም ባለድርሻ አካላት የትምህርት ቤቶችን የመሠረተ ልማትና የግብዓት እጥረቶች ለመቅረፍ እንዲሁም አንድም ተማሪ ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዳይቀር የማድረግ ተግባርን በኃላፊነት ሊተገብሩ እንደሚገባም አሳስበዋል። በዞኑ የተማሪዎች ምዝገባን እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በማጠናቀቅ ትምህርትን በወቅቱ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑም ተመልክቷል። በመድረኩም የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የትምህርት ቤተሰቦች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።  
ኢኮኖሚ
የመገጭ ግድብ የመደመር መንግስት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅም ማሳያ ነው
Aug 25, 2026 156
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦የመገጭ ግድብ የመደመር መንግስት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅም ማሳያ መሆኑን የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ገለጹ። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የመገጭ ግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ተቋማት ለተውጣጡ ጋዜጠኞች አስጎብኝቷል። የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፤የመገጭ ግድብ የጎንደር ከተማ የዘመናት ጥያቄ መሆኑን ገልጸዋል። የመገጭ ግድብ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለሕዝቡ ያልተሠራውን ተሠራ እየተባለ 18 ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰዋል። መገጭ ለንጹህ መጠጥ ውሃና ለመስኖ ልማት በመዋል ለኢትዮጵያ ብዙ ጥቅም ማስገኘት የሚችል ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ነገር ግን ፕሮጀክቱ በአግባቡ ባለመመራቱ፣ በጋ ላይ የተሠራው ክረምት ላይ በጎርፍ እየተናደ ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሕልውና ሥጋት፣ ለጣና ሐይቅ ደግሞ በደለል መሞላት ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ብለዋል። ይሁን እንጂ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ሰጭነት ፕሮጀክቱን እንደገና በማጥናት ሕዝብ ከባዶ ተስፋ ወደሚጨበጥ ሕልም ማምጣት እንደተቻለ ገልጸዋል። ይህም ለሕዝቡ ከሚሰጠው ቀጥተኛ ጥቅም ባለፈ፣ ዓባይ ወንዝና ጣና ሐይቅን ከደለል በመታደግ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት እንዳለው በተግባር ገልጧል ብለዋል። በመገጭ ግድብ ግንባታ የታየው ፈጣን የግንባታ ለውጥ የመደመር መንግሥት ፕሮጀክት ጀምሮ በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅሙን በተግባር ያሳየበት መሆኑን ገልጸዋል። የመገጭ ግድብ ሰፊ የእርሻ መሬት ላለው የደንቢያ አካባቢ የልማት ተስፋ፤ ለጎንደር ከተማ ደግሞ የዘላቂ ንጹህ መጠጥ ውሃ ብስራት ይሆናል ብለዋል። ሕብረተሰቡ የግድቡን አስፈላጊነት በወጉ በመረዳት አካባቢውን በንቃት እየጠበቀ፣ የፕሮጀክቱን አፈጻጸም በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን ገልጸዋል። ለ18 ዓመታት ሕዝቡን በባዶ ተስፋና በጎርፍ ሲያማርር የነበረው የመገጭ ግድብ፣ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ በቅርቡ ይጠናቀቃል ብለዋል።  
የአፍሪካን የጤና ሥርዓት በራስ አቅም ለማዘመን የአባል ሀገራትን ትብብር ማጠናከር አስፈላጊ ነው
Aug 25, 2026 201
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካን የጤና ሥርዓት በራስ አቅም ለማዘመን ኢንቨስትመንትንና የአባል ሀገራትን ትብብር ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር መሐመድ ያኩብ ጃናቢ ገለጹ። 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ኮሚቴ ጉባኤ በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር መሀመድ ያኩብ ጃናቢ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ 76ኛ የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ኮሚቴ ጉባኤ በአንድ መድረክ ከመወያየት በላይ ነው። መድረኩ የአፍሪካ የጤና ችግሮች ላይ የጋራ ውይይት በማድረግ የጋራ የመፍትሔ ሀሳብ የሚፈልቅበት መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካ በመሪዎች ቁርጠኝነት፣ በጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ዝግጅት እንዲሁም በማህበረሰቡ ትብብር በጤና ስርዓቱ ላይ መሻሻል ታይቷል ብለዋል። አፍሪካ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን በላይ ህዝብ ምድር መሆኗን በማንሳትም፤ አፍሪካ የጤና ስርዓቷን በራሷ አቅም ለመገንባት ጠንካራና ቀጣይነት ያለው የጤና ተቋማትን መገንባት ይገባታል ነው ያሉት። በአፍሪካ ለተመዘገበው የጤና አገልግሎት መሻሻል የዓለም ጤና ድርጅት ያልተቋረጠ ድጋፍ ማድረጉን በመግለፅ፤ የአፍሪካ የጤና ኢንቨስትመንትን በራስ አቅም መፍጠር አስፈላጊ ነው። የአፍሪካ ራዕይ ግልጽ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የጤና ልህቀት ማዕከል መገንባትና የጤና ስርዓቷን በራሷ አቅም መገንባት መሆኑን በመግለጽ። አህጉሪቱ የዕወቀትና የተፈጥሮ ሀብት ችግር የለባትም፤ መሰረታዊው ጉዳይ ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችል የጤና አገልግሎት መስጠት ነው ሲሉም ገልጸዋል። የጤና ሥርዓት ዝማኔ አመራር፣ ኢንቨስትመንትና ትብብር እንደሚጠይቅ ጠቁመውም፤ የዓለም ጤና ድርጅት አፍሪካ አቅሟን እንድትገነባ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።  
የመገጭ ግድብ ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ደርሷል
Aug 25, 2026 133
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው የመገጭ ግድብ ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ መድረሱን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ የመገጭ የግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ለተውጣጡ ጋዜጠኞች አስጎብኝቷል። ሚኒስቴሩ የኢትዮጵያን በምግብ ራስን የመቻል ጉዞ የሚያሳኩ የመስኖ ልማት መሰረተ ልማቶችን እያስፋፋ ይገኛል። ከእነዚህ መሰረተ ልማቶች መካከል በአማራ ክልል ጎንደር አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው መገጭ ግድብ አንዱ ሲሆን ግድቡ ከተጀመረ ረዘም ያለ ጊዜ አስቆጥሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ግድቡ በፍጥነት ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረትም በተለይ ባለፉት ሁለት ዓመታት ግድቡን ለማጠናቀቅ በተደረገው ርብርብ አሁን ላይ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ደርሷል። በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የመስኖ ፕሮጀክቶች ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ እንጂነር አሸናፊ ሊካሳ በሰጡት ማብራሪያ ግንባታው በመጓተቱ ምክንያት ግንባታውን ይዞ የነበረው ተቋራጭ በአዲስ እንዲተካ መደረጉን አንስተዋል። አሁን ላይም ግድቡን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ሁሉን አቀፍ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል። የውሃ መስኖ መቆጣጠሪያው ሲቪል ስራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ጠቁመው፤ የኤሌክትሮ መካኒካል ስራው በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ግድቡ በአሁኑ ወቅት ውሃ መያዝ መጀመሩን ጠቅሰው፤ እስካሁን 33 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ መያዙንም ተናግረዋል። የግድቡ ግንባታ 94 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ የግዱቡ የውሃ ማስተንፈሻ ስፒልዌይ ስራም መጠናቀቁን ገልጸዋል። የግድቡ ግንባታ መሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በርካታ ነዋሪዎችን በመስኖ ልማትና በመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተናግረዋል።
የደባርቅን የመልማት ፀጋ ወደ ተጨባጭ አቅም ለመቀየር ከተማዋን በመሰረተ ልማት ማበልጸግ ይገባል - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Aug 24, 2026 373
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦የደባርቅን የመልማት ፀጋ ወደ ተጨባጭ አቅም ለመቀየር ከተማዋን በመሰረተ ልማት ማበልጸግ እንደሚገባ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የደባርቅን ከተማ ለማልማት የተዘጋጀ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር "ደባርቅን እናሳምር ከተማችንን እናድምቅ" በሚል መሪ ሀሳብ በሂልተን ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል። በመርሃ ግብሩ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሀብቶች ተገኝተዋል። በገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ "ኑ ተፈጥሮ የገለጠችውን ድንቅ የቱሪስት መስህብ የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መግቢያ በር የሆነችውን ደባርቅ ከተማ በጋራ እናልማ" የሚል ጥሪ ቀርቧል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ደባርቅ የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መግቢያ ከተማ ናት። ይሁን እንጂ ደባርቅ የታሪክ ባለቤትነቷን፣ የቱሪዝም መተላለፊያነቷን የሚመጥን ልማት አልታደለችም ብለዋል። የደባርቅን የመልማት ፀጋ ወደ ተጨባጭ አቅም መለወጥ የሚያስችል እንቅስቃሴ መጀመሩንም ጨምረው ገልጸዋል። በመሆኑም ከተማዋን በማልማት የተፈጥሮ ውበቷን ለመግለጥ ሁሉም በጋራ ትብብር ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። የደባርቅ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ ጌትነት ፀጋየ በበኩላቸው፤ ደባርቅ የቀድሞ የሰሜን አውራጃ ከተማ፣ በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መገኛ የቱሪዝም ቀዬ መሆኗን ገልጸዋል። ደባርቅ በተፈጥሮ ሀብቶች የበለጸገች የቱሪዝም ማዕከል ብትሆንም የሚገባትን ያህል መልማት ባለመቻሏ የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ ማራዘም አልቻለችም ነው ያሉት። ስለሆነም መንግሥት ያመጣው የኮሪደር ልማት ተቋዳሽ እንድትሆን ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ማዕከላቱ በሽታና ሙቀትን የሚቋቋሙ የስንዴ ዝርያዎችን በማውጣት የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደጉ ነው
Aug 25, 2026 144
አዳማ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፡-የግብርና የምርምር ማእከላት በቆላማ አካባቢዎች በሽታና ሙቀትን የሚቋቋሙ የስንዴ ዝርያዎችን በምርምር በማውጣት የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደጉ መሆናቸውን የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ። ብሔራዊ የዘር ብዜትና አጠቃቀም የአሰልጣኞች ሥልጠናና የባለድርሻ አካላት ምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ንጉሤ ደቻሳ እንዳሉት፤ የግብርና ምርምር ማዕከላት የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ፣ በማስተዋወቅ እንዲሁም ዘርን በማባዛት ለግብርና ምርትና ምርታማነት ማደግ ከፍተኛ ድርሻ እያበረከቱ ይገኛሉ። ለዚህም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በቆላማ አካባቢዎች በሽታና ሙቀትን የሚቋቋሙ የስንዴ ዝርያዎችን በምርምር በማፍለቅና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች በማቅረብ ረገድ ያደረጉት ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።   የስንዴ ሰብሎቹም በቆላማ አካባቢዎች በሽታንና ሙቀትን በመቋቋም የአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚነት ማሳደጋቸውን አስታውቀዋል። በዚህ ረገድ የአፍሪካ የግብርና ቴክኖሎጂ ማሸጋገሪያ ፕሮጀክት የመስኖ ስንዴ ቴክኖሎጂዎችን የማቅረብ እና መነሻ ዘሮችን የማባዛት ሥራን ሲደግፍ መቆየቱን ጠቁመዋል።   በኢንስቲትዩቱ የፕሮጀክቱ አስተባባሪና የቁሉምሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ዓለማየሁ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ በተደረገባቸው በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በአፋር ክልሎች የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ አዎንታዊ ውጤት ማስገኘቱን ተናግረዋል። በዚህም የአርሶ አደሩን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሻሻል አማካይ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በሄክታር 40 ኩንታል ማድረስ መቻሉንም አስረድተዋል።   ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደጀኔ ሂርጳ፤ ከግብርና ምርምር የሚወጡ የስንዴ ዝርያዎች በሽታን የመቋቋም አቅማቸውና ምርታማነታቸው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በፕሮጀክቱ ተሻሽለው የወጡ አዳዲስ ዝርያዎች በክልሉ በሄክታር የሚገኘውን ምርት 40 ኩንታል ማድረሳቸውንም አስረድተዋል።   ከፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች መካከል በአርሲ ዞን የሄጦሳ ወረዳ አርሶ አደር አበራ ደገፋ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የስንዴ ቴክኖሎጂን ተደራሽ በማድረጉ ምርታማነታቸውን በእጥፍ ማሳደግ እንደቻሉም ተናግረዋል።        
በክልሉ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል
Aug 25, 2026 102
አርባምንጭ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡ "የእንስሳት ዝርያን ማሻሻል ለላቀ ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በክልሉ የ2019 በጀት ዓመት የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ስራ ማስጀመሪያ ስነ ስርአት በጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ተካሂዷል።   በስነ ስርአቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) እንደገለጹት በክልሉ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል ምርታማነትን በማሳደግ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል፡፡ በክልሉ የእንስሳት ምርታማነት በመጨመሩም የምግብ ሉዐላዊነትን ለማረጋገጥ አቅም መፍጠሩን አመልክተዋል። በክልሉ ሰፊ የእንስሳት ሀብት መኖሩን የጠቀሱት መሪሁን ( ዶ/ር ) የእንስሳት ሀብትን በአግባቡ በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማላቅ የሚከናወኑ ተግራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡ የእንስሳትን ዝርያ ማሻሻል ስራው በወተት ሀብትና በዝርያ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያስገኝ መሆኑን ጠቅሰው የክልሉን አርሶና አርብቶ አደር ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚከናወኑ ተግባራት ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።   የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዞኑ የምግብ ሉዐላዊነት እንዲረጋግጥ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ ነው ብለዋል። በዞኑ የወተት ምርታማነት በመጨመሩ ማህበረሰቡ ጥሪት ከማፍራት ባለፈ የአመጋገብ ስርዓቱ ላይ ጉልህ ለውጥ ማሳየቱን ጠቅሰዋል። እንደ ክልል የተጀመረውን የእንስሳት ዝርያ በማሻሻል ምርታመነትን የማሳደግ መርሃ ግብር በሁሉም ወረዳዎችና ቀበሌዎች ተግባራዊ ለማድረግ በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። በዞኑ በሁሉም አካባቢ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ለማስፋፋት በተከናወኑ ተግባራት 500 የወተት መንደሮች ተፈጥረዋል ያሉት ደግሞ የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ ማጌሶ ማሾሌ ናቸው።   የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።  
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኤአይ፣ የዲጂታል ጤና እና የአረንጓዴ ልማት ራዕይ የሚደነቅ ነው -በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ
Aug 24, 2026 458
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰው ሠራሽ አስተውሎትን (AI) እና የዲጂታል ጤና ቴክኖሎጂዎችን ከሀገራዊ የልማት እንቅስቃሴዎች ጋር በማቀናጀት እያከናወኑ ያሉትን አርቆ አሳቢነትን የተከተሉ ስራዎች የሚደነቁ መሆናቸውን በዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ፍራንሲስ ቺሳካ ካሶሎ ገለጹ። ሀገራዊ የልማት እንቅስቃሴዎቹ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን፣የከተሞች ማዘመን እና የወንዞች ዳርቻ ልማት ስራዎችን ያካተቱ ናቸው። በኢትዮጵያ፣በአፍሪካ ህብረት እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፍራንሲስ ቺሳካ ካሶሎ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ የማህበረሰብ ጤና ተደራሽነትን በማስፋት ሂደት ውስጥ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ረገድ ግንባር ቀደም ሀገር ናት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአፍሪካ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና አምባሳደር ናቸው፤ በዚህም ከአፍሪካ ህብረት እውቅና እና ሽልማት አግኝተዋል ብለዋል። ተወካዩ አክለውም በጤናው ዘርፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት በሚደረገው ጥረት የዓለም ጤና ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግስት እና ከጤና ሚኒስቴር ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የአየር ጥራትን ማሻሻል እና ደህንነቱ የተጠበቀ አካባቢን መፍጠር የመተንፈሻ አካላት በሽታዎችን እና የካንሰር ስጋቶችን እንደሚቀንስ በመግለጽ፣ የአካባቢ ጥበቃ ፖሊሲዎች ለህዝብ ጤና ወሳኝ ምሰሶ መሆናቸውን አስረድተዋል። ከዚህ አኳያም የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እና የከተማ ልማት ተግባራት ከጤና ጥበቃ እና ቅድመ-መከላከል ስራዎች ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። አረንጓዴ አሻራ የአየር ጥራትን ያሻሽላል፤ ንጹህ አየር ደግሞ ለተሻለ ጤንነትና የመተንፈሻ አካላት በሽታዎችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ሲሉ አስረድተዋል። የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት የአካባቢ ጽዳትና ንፅህናን በማስጠበቅ ረገድ ያለውን የጤና ጥቅም በአጽንኦት አንስተዋል። የኮሪደር ልማቱ የአካባቢ ጽዳትን እንደሚያሻሽል የጠቆሙት ተወካዩ፣ ስራው በሀገር አቀፍ ደረጃ መስፋቱ በውሃ ወለድ አምጪ ተህዋሲያን የሚመጡ በሽታዎችን እንደሚቀንስ አመልክተዋል። መንግስት የከተሞችን ውበት ከማስጠበቅ ባለፈ የአየር ጥራትንና የህዝብን ጤና ለመጠበቅ በአረንጓዴ መሰረተ ልማቶች ላይ እያፈሰሰ ያለው ሀብትና የሰጠው ትኩረት ሊደነቅ የሚገባው ነው ብለዋል። በአረንጓዴ መሰረተ ልማት እና ጤናማ ከተሞች (healthy cities) እንዲሰፉ የሚያፈሰው መዋዕለ ንዋይ ከተሞችን ከማስዋብ ባሻገር፣ የህዝብን ጤና በዘላቂነት ለመጠበቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ነው የገለጹት። በዚህ ረገድም መንግስት ትኩረቱን ከህክምና ወጪ ይልቅ በሽታን ወደ መከላከል አቅጣጫ በማዞር በቅድመ-መከላከል ስራዎች ላይ እያከናወነ ያለውን ስራ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በመላው አፍሪካ ሊደገም እንደሚገባ ተወካዩ አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኤሮስፔስ ዘርፍን ለማሳደግ እና ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያስችል ጠንካራ መሠረት እየጣለ ነው
Aug 21, 2026 650
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኤሮስፔስ ዘርፍን ለማሳደግ እና የወደፊት ሙያተኞች ማፍራት የሚያስችል ጠንካራ መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ላዕከ ታደሰ ገለጹ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከቦይንግ ኩባንያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ "STEM" ትምህርት ሥልጠና መርሐ ግብር ያጠናቀቁ የምረቃ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።   የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ላዕከ እንደገለጹት፤ ከተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች የተወጣጡ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በ"STEM" የትምህርት መርሃ ግብር አማካኝነት የስድስት ሳምንታት ሥልጠና ሲከታተሉ ቆይተዋል። ተማሪዎቹ በቆይታቸው ከቴክኒክ እውቀት ባሻገር የቡድን ሥራ፣ ሂሳዊ አስተሳሰብ፣ ችግር ፈቺነት እና የፈጠራ ክህሎትን ማዳበር የሚያስችላቸው ሥልጠና መከታተላቸውን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያን የኤሮስፔስ ዘርፍ ለማሳደግ እና የነገ የሀገሪቷን ባለሙያዎች ለማፍራት የሚያስችል ጠንካራ መሰረት እየተጣለ መሆኑንም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ላዕከ ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ ሲሆን፤ ከቦይንግ ኩባንያ ጋር ለረጅም ዓመታት የቆየ የንግድ እና የቴክኒክ ትብብር እንዳለው ይታወቃል።
ስፖርት
ማንችስተር ዩናይትድ ለአመታት ሲፈልገው የነበረውን ካርሎስ ባሌባን አስፈረመ
Aug 25, 2026 154
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ማንችስተር ዩናይትድ የካሜሮኑን አማካይ ካርሎስ ባሌባን ከብራይተን በ70 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረሙን ዛሬ አስታውቋል። የ22 ዓመቱ ተጫዋች በኦልድ ትራፎርድ ለቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራት የተፈራረመ ሲሆን፣ እስከ እ.አ.አ 2031 በሚቆየው በዚህ ውል ላይ የክለቡ ተጨማሪ የ12 ወራት የማራዘም አማራጭ ተካቷል። ባሌባ ወደ አዲሱ ክለቡ መቀላቀሉን አስመልክቶ በሰጠው አስተያየት፣ ለረጅም ጊዜ ለመቀላቀል ሳልመው በነበረው ማንችስተር ዩናይትድ መፈረም በመቻሌ ታላቅ ደስታና ክብር ይሰማኛል ብሏል። ከአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ጋር በመስራት እና የእሱን ልምድ በመጠቀም ብቃቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚፈልግም ገልጿል። ባሌባ በማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ስር በክረምቱ የዝውውር መስኮት የፈረመ ሶስተኛው የአማካይ ተጫዋች ሆኗል። ዩናይትድ ቀደም ሲል አንድሬ ሳንቶስን ከቼልሲ በ48 ሚሊዮን ፓውንድ እና ዩሪ ቲሊማንስን ከአስቶንቪላ በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረሙ ይታወቃል።
ቼልሲ የውድድር ዓመቱን በድል ጀምሯል
Aug 24, 2026 283
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት የመጨረሻ መርሐ ግብር ቼልሲ ፉልሃምን 3 ለ 2 አሸንፏል። ማምሻውን በክራቫን ኮቴጅ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጆአኦ ፔድሮ፣ ሞርጋን ሮጀርስ እና ኮል ፓልመር የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ጆአኦ ፔድሮ በ31ኛው ሴኮንድ ያስቆጠረው የዓመቱ ፈጣን ጎል ሆኖ ተመዝግቧል። ጆሹዋ ኪንግ እና ጎንዛሎ ጋርሺያ የፉልሃምን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በ117 ሚሊዮን ፓውንድ ከአስቶንቪላ ወደ ቼልሲ የተዘዋወረው ሞርጋን ሮጀርስ በመጀመሪያ የሊግ ጨዋታው ጎል አስቆጥሯል። ከሪያል ማድሪድ ፉልሃምን የተቀላቀለው ጎንዛሎ ጋርሺያም የመጀመሪያ የሊግ ጎሉን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጨዋታው እጅግ አዝናኝና በርካታ የግብ እድሎች የተፈጠሩበት ነበር። የቼልሲው አሰልጣኝ ዣቪ አሎንሶ በመጀመሪያ ጨዋታው ድል ቀንቶታል። በአንጻሩ አዲሱ የፉልሃም አዲሱ አሰልጣኝ አርቫሎ አርቤሎአ በመጀመሪያ የሊግ ጨዋታቸው ሽንፈት አስተናግዷል። ጨዋታውን ተከትሎ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ተጠናቋል። የሁለተኛ ሳምንት የሊጉ ጨዋታዎች ከአርብ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳሉ።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስ ሽንፈትን አስተናገደ
Aug 24, 2026 165
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ የምድብ ሁለት መርሐ ግብር የዩጋንዳው ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በኪጋሊ ፔሌ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አግነስ ናቡኬንያ በ11ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ግቧን አስቆጥራለች። በአሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው የሚመራው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሽንፈቱን ተከትሎ ወደ ግማሽ ፍጻሜ የማለፍ እድሉ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል። ንግድ ባንክ በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታው የጅቡቲውን ኡጄኮን 11 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ቡድኑ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ለማለፍ በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስን በኡጄኮ መሸነፍ ይኖርበታል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ረቡዕ ነሐሴ 2018 ዓ.ም በኪጋሊ ፔሌ ስታዲየም ይካሄዳል። ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስ በጨዋታው ካሸነፈ ወይም አቻ ከወጣ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ያልፋል። የካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ከነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሩዋንዳ ኪጋሊ እየካሄደ ይገኛል። በውድድሩ ላይ 10 ክለቦች በሶስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛል። የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ውድድሩን ያሸነፈው ክለብ ዞኑን ወክሎ በሻምፒዮንስ ሊጉ መሳተፉን ያረጋግጣል። የሴካፋ ማጣሪያ እስከ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
አካባቢ ጥበቃ
በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራና የተፈጥሮ ጥበቃ ስራዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚደረገውን እንቅስቃሴ እያገዙ  ነው
Aug 24, 2026 229
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራና የተፈጥሮ ጥበቃ ስራዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚደረገውን እንቅስቃሴ እያገዙ እንደሚገኙ የክልሉ ደን እና ዱር እንስሳት ድርጅት አስታወቀ። በክልሉ ደረጃ እየተካሄደ ያለው የካርበን ሽያጭ በአለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ተገልጿል። የኦሮሚያ ክልል ደን እና ዱር እንስሳት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አራርሳ ረጋሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ክልሉ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በተለይም የካርቦን ዳይኦክሳይድ ልቀትን በመቀነስ የምድር ሙቀትን ለመግታትና የደን ሽፋን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ አመላክተዋል።   በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተተከሉት ችግኞች መካከል አብዛኞቹ ጸድቀው ወደ ደንነት በመሸጋገራቸው የአካባቢውን አየር ንብረት በመጠበቅና የካርቦን ልቀትን በመቀነስ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበሩከቱ ይገኛሉ ብለዋል። ህብረተሰቡም ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ዘላቂ ተጠቃሚ የሚሆንበት አሰራር ተዘርግቶ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የመቋቋም አቅምን የማጠናከሩ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት። አቶ አራርሳ ጨምረው እንደገለጹት፤ ክልሉ የደን ካርበን ንግድን በማስፋፋት በአለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በተደረገው ሳይንሳዊ ጥናት መሠረት አንድ ሄክታር የደን መሬት ከ10 እስከ 20 ቶን የሚደርስ ካርቦን ዳይኦክሳይድ በውስጡ የመያዝ እና የማመቅ ከፍተኛ አቅም እንዳለው አብራርተዋል። ይህም ክልሉ የሚያካሂደው የደን ልማት ለአለም አቀፉ የካርቦን ልቀት ቅነሳ ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ማረጋገጫ እንደሆነ አብራርተዋል። አቶ አራርሳ ኢትዮጵያ ከካርቦን ገበያ ገቢ ማግኘት የጀመረችበትን ታሪካዊ ሂደት ሲያብራሩ፤ የመጀመሪያው የደን ካርበን ሽያጭ እ.ኤ.አ በ2012 በባሌ ደን መጀመሩን አውስተዋል። እ.ኤ.አ ከ2012 እስከ 2019 ባለው ጊዜ ውስጥም 9 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ካርቦን ለገበያ በማቅረብ ወደ ግማሽ ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ ተገኝቷል።   ከሽያጩ የተገኘው ገቢም ደኑን ለጠበቁ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ለቀጣይ የደን ልማት ስራዎች በመዋሉ የማህበረሰቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል። ድርጅቱም ከአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ አጋሮች ጋር በመቀናጀት እ.ኤ.አ ከ2022 እስከ 2024 ባሉት ዓመታት የተመዘገበውን 13 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የካርቦን መጠን ለገበያ ለማቅረብ ዝግጁ ሆኗል። በቀጣይም የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ደኖችን በሳይንሳዊ መንገድ በመንከባከብና የካርቦን ንግድን በመተግበር የአካባቢ ጥበቃውን እንዲሁም ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን የማሳደግ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።    
ውበትን ከስልጣኔ ጋር ያቆራኙ የኮሪደርና የወንዝ ዳር ልማቶች
Aug 23, 2026 269
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ በኮሪደር እና በወንዝ ዳር ልማቶች የተገነቡት ቤተ መጽሐፍት እና የተለያዩ የመዝናኛ ስፈራዎች ለመጪው ትውልድ ብሩህ ተስፋን የሰነቁ የስልጣኔ ማሳያዎች መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መዲናዋን ዓለም አቀፍ ደረጃዋን የጠበቀች፣ ለነዋሪዎቿ ምቹና ዘመናዊ ለማድረግ እያከናወነ የሚገኘው ግዙፍ የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ በማህበረሰቡ የዕለት ተዕለት የኑሮ ዘይቤ ላይ አዎንታዊ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። ይህ በዋና ዋና አደባባዮች፣ መናፈሻዎች፣ መንገዶችና የወንዝ ዳርቻዎች ላይ ያተኮረው የመሠረተ ልማት ዝርጋታ፤ ውበትን ከጥቅም ጋር አዋህዶ የያዘ በመሆኑ ከፍተኛ ለውጦችን እያመጣ ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሉት፤ የተገነቡት የመጫወቻና የማንበቢያ ስፍራዎች የከተሜነት ምህዳሩን ከማሻሻላቸው ባሻገር ለወጣቶች የማሰላሰያና አዳዲስ ሐሳቦችን ማፍለቂያ ማዕከላት እየሆኑ ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ወይዘሮ ጺዮን ጌታቸው፤ በቅርብ ዓመታት የተከናወኑት የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች አዲስ አበባን ለኑሮ ተስማሚ ከማድረጋቸው ባሻገር፣ ነዋሪው አእምሮውን እያዝናና እውቀት እንዲገበይበት መንገድ መክፈታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ግርማ አለሙ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቶቹ መጪውን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉና ለአዲሱ ትውልድ ጠንካራ መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ጠቁመው፣ በተለይም የተዘጋጁት የንባብ ማዕከላት ለተለያዩ ጥናትና ምርምሮች ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ተናግረዋል።   የመዲናዋ ነዋሪ ወጣት ፍራኦል ናትናኤል በበኩሉ የኮሪደር ልማቱ የሀገሪቱን መልካም ገጽታ በመገንባት በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው ብሏል።   ይህም ለአገር ውስጥና ለውጭ ኢንቨስትመንት መሳብ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጿል።   አቶ እንዲሪስ ተሾመ እና አቶ ግርማ ንጉሴ የተባሉ ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፤ በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ ደረጃቸውን የጠበቁ በርካታ የመዝናኛ ስፍራዎች ተገንብተዋል ብለዋል። አሁን ላይ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የእረፍት ጊዜ ለማሳለፍ እነዚህን አካባቢዎች ምርጫቸው ማድረጋቸውን ተናግረዋል።   የወንዝ ዳርቻ ልማቶቹ፣ የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍትና የመዝናኛ ስፍራዎቹ የከተማዋን ውበትና የህዝቡን የማህበራዊ ህይወት ደረጃ ያሳደጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።    
አካባቢን ከብክለት በመጠበቅ ጤናማና አምራች ዜጋን የማፍራቱ ተግባር ይጠናከራል
Aug 21, 2026 358
ገንዳውሃ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፡- ህብረተሰቡ አካባቢውን ከብክለት በመጠበቅና በማፅዳት ጤናማና አምራች ዜጋን የማፍራት ተግባርን አጠናክሮ እንዲቀጥል የምዕራብ ጎንደር ዞን አካባቢና ደን ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በገንዳውኃ ከተማ አስተዳደር "ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የሀገራዊ እንቅስቃሴ አካል የሆነ የፅዳት ዘመቻ ዛሬ ተካሄዷል።   የምዕራብ ጎንደር ዞን አካባቢና ደን ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ መልካም ዋሲሁን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ፅዱና ውብ አካባቢን መፍጠር ለጤናማ ማኅበረሰብ ግንባታ መሠረት ነው። አካባቢን ከፕላስቲክና ከሌሎች ደረቅ እንዲሁም ፈሳሽ ቆሻሻዎች ነፃ በማድረግ ፅዱ አካባቢን መፍጠር አምራች፣ ጤናማና ውጤታማ ትውልድ ለማፍራት ወሳኝ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል። ለዚህም ማኅበረሰቡ የአካባቢ ፅዳት ሥራን የአንድ ወቅት ዘመቻ ሳያደርግ የዘወትር ተግባርና የኑሮ ባህሉ በማድረግ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አሳስበዋል። የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ጉርባ በበኩላቸው፣ ከአካባቢ ንፅህና ጉድለት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል ሕብረተሰቡ የግልና የአካባቢውን ንፅህና ዘወትር ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል። አካባቢው ሞቃታማ በመሆኑ እንደ ወባ፣ ኮሌራና መሰል ተላላፊ በሽታዎች በወረርሽኝ መልክ እንዳይከሰቱ የግልና የአካባቢን ንፅህና መጠበቅ ባህል ሊደረግ ይገባል ነው ያሉት። የገንዳውኃ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተወካይ አቶ አዳነ ሀሰን እንዳሉት፣ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹና ለባለሀብቶች ሳቢ ለማድረግ በአካባቢ ንፅህና አጠባበቅ ላይ በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል። የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የንግዱ ማኅበረሰብና የወጣት አደረጃጀቶች አካባቢያቸውን ሰላም ከመጠበቅ ጎን ለጎን ፅዱና ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ የጀመሩትን ተሳትፎ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል። "ለነገው ሀገር ተረካቢ ሕፃናት ፅዱ ከተማን ማስረከብ የእኛ የወጣቶች ኃላፊነት ነው" ያለው ደግሞ በፅዳት ዘመቻው የተሳተፈው ወጣት ሃብታሙ አክሊሉ ነው። ከተማዋን ከፕላስቲክና ከሌሎች መርዛማ ኬሚካሎች በማፅዳት ማራኪና ለነዋሪዎቿ የምትመች ተመራጭ ከተማ ለመፍጠር በሚደረገው ሂደት በቀጣይም የድርሻውን እንደሚወጣ አረጋግጧል። በፅዳት ዘመቻው የከተማዋ የመንገድ ዳርቻዎች፣ የገበያ ስፍራዎችና የሕዝብ መዝናኛ አካባቢዎችን ከቆሻሻ ፅዱ የማድረግ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፣ በየሳምንቱም የፅዳት ዘመቻው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ከወጣው መርሃ ግብር ለመረዳት ተችሏል። በተካሄደው የፅዳት ዘመቻም የዞኑና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የመንግሥት ሰራተኞች፣ የአካባቢው ነዋሪዎችና የተለያዩ አደረጃጀቶች ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያ በሰው እና በአካባቢ ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ የማይመክኑ ኦርጋኒክ በካዮችን ለመቆጣጠርና ለማስወገድ በትኩረት እየሰራች ነው
Aug 21, 2026 345
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሰው እና በአካባቢ ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ የማይመክኑ ኦርጋኒክ በካዮችን (POPs) ለመቆጣጠርና ለማስወገድ በትኩረት እየሰራች መሆኑን የኢፌዴሪ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የተሻሻለ የብሔራዊ የትግበራ እቅድ ሰነድ ግምገማ እና ማጽደቂያ መድረክ አካሂዷል።   የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በዚሁ ወቅት፤ የማይመክኑ ኦርጋኒክ በካዮች በባህሪያቸው ቶሎ የማይበሰብሱ፣ በሰው እና በአካባቢ ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ቁሶች ናቸው ብለዋል። ከእነዚህ ውስጥም ዲዲቲ (DDT)፣ ፒፎስ (PFOS) እና ፒኤፍኤችኤክስኤስ (PFHxS) የተሰኙትን ለአብነት አንስተዋል። የማይመክኑ ኦርጋኒክ በካዮች (POPs) የሚያስከትሉትን ጉዳት ለመከላከልና ለማስወገድ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ወይም እንዳይመረቱ የሚያደርግ እኤአ በ2001 የስቶክሆልም ስምምነት መደረጉን አውስተዋል። ኢትዮጵያ ስምምነቱን መሰረት በማድረግ በሰው እና በአካባቢ ላይ ጉዳት የሚያመጡ የማይመክኑ ኦርጋኒክ በካዮችን (POPs) ለመቆጣጠርና ለማስወገድ ዘርፈ-ብዙ ተግባራትን እንዳከናወነች ጠቁመዋል። ከዚህ ቀደም ለተለያዩ አላማዎች በሚል ይመረቱ የነበሩ እንደ ዲዲቲ (DDT) ያሉ የማይመክኑ በካዮች እንዳይመረቱ እንዲሁም ሀገር ውስጥ ማምከኛ የሌላቸው የተለያዩ ኬሚካሎችን ወደ ውጭ በመላክ እንዲመክኑ መደረጉን አስታውቀዋል። ዛሬ ለምክክር የቀረበው ሰነድ በሀገር ደረጃ የማይመክኑ ኦርጋኒክ በካዮች አያያዝ፣ ቁጥጥር እና አስተዳደርን የሚያጠናክር ተግባራዊ የስራ መመሪያ መሆኑን ገልጸዋል። መድረኩ አሁን በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ካለው ሶስተኛ ዙር "ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" ስራ ጋር ተያያዥነት ያለው እንደሆነም አመላክተዋል።   ለብሔራዊ ትግበራ መርሃ ግብሩ ስኬት የፌደራልና የክልል ተቋማት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበራት እና የልማት አጋሮች ቅንጅት ወሳኝ መሆኑንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ ጨምረው ተናግረዋል። አዳዲስ በካይ ኬሚካሎችን መለየት፣ የላቦራቶሪ ቁጥጥር አቅምን ማሳደግ፣ ማምከኛ መሳሪያዎችን መታጠቅ፣ የመረጃ ስብሰባን ማጠናከርና የቴክኒክ እንዲሁም የፋይናንስ አቅምን ማጎልበት የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው ብለዋል። ከመድረኩ የተገኙት ግብዓቶችን በማካተት ሰነዱን የበለጠ ለማጠናከርና ውጤት ተኮር ለማድረግ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 1276
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 1039
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 1315
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1897
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
የአረንጓዴ አሻራ ስኬት፦ኢትዮጵያን የአየር ንብረት ጥበቃ ሞዴል ያደረገ ኢኒሼቲቭ
Aug 23, 2026 322
የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ የተጀመረው በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ነው። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እስከ አሁን ከ54 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እ.አ.አ በ2027 በኢትዮጵያ በሚካሄድበት ወቅት የተተከሉ ችግኞችን ብዛት 65 ቢሊዮን የማድረስ እቅድ ተይዞ እየተሠራ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች ያሉት ነው።ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የምግብ ምርታማነትን በማሳደግ፣ የደን ሽፋንን በመጨመር፣ የተራቆተ መሬትን ወደ ነባር ይዞታው እንዲመለስ በማድረግ እና አይበገሬ የአረንጓዴ ኢኮኖሚን በመገንባት ረገድ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። በዚህም በ2011 ዓ.ም 17.2 በመቶ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን፣ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በተከናወነው ሥራ ወደ 23.6 በመቶ ማደግ ችሏል።   ይህ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እውቅና አግኝቷል።በሁለተኛው የዓለም የምግብ ሥርዓት ጉባኤ እንዲሁም በአዲስ አበባ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ ሥራዋን ያስተዋወቀች ሲሆን፣ የአፍሪካ ሀገራትም ለአህጉሪቱ ትልቅ ተምሳሌት የሚሆን ኢኒሼቲቭ ሲሉ አድንቀውታል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታዘጋጅ መመረጧ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እያከናወነች ላለው ጥረት ዓለም አቀፍ እውቅና የተሰጠበት እና የሀገሪቱን የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ውጤት የሚያሳይ ነው። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በመለገስ የአካባቢ ጥበቃ የጋራ አጀንዳ መሆኑን በተግባር አሳይታለች።ይህም አረንጓዴ ዲፕሎማሲ በሀገራት መካከል በጎ ግንኙነትንና አዎንታዊ የቀጣናዊ ትስስር ድልድይን እየገነባ ይገኛል። የድንበር ተሻጋሪ የወንዝ ተፋሰሶችን በመንከባከብ፣ የታዳሽ ኃይል አቅርቦትን ለጎረቤት ሀገራት በማዳረስ እና በጋራ ድንበሮች አካባቢ የደን ሽፋንን በማሳደግ ረገድ እያከናወነችው ያለው ሥራ አህጉራዊ ሰላምና ትብብርን የሚያጎለብት አዲስ የዲፕሎማሲ መንገድ ከፍቷል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች የአህጉሪቱን ፍላጎትና ጥቅም ለማስከበር ግንባር ቀደም ተሟጋች ሆናለች።   ለአየር ንብረት ለውጥ አነስተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ነገር ግን ለጉዳቱ በከፍተኛ ሁኔታ የተጋለጡ የአፍሪካ ሀገራት ፍትሃዊ የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ እንዲያገኙ ድምፅ በመሆን አህጉራዊ መሪነቷን አስመስክራለች። ይህም አፍሪካውያን በራሳቸው ሀገር በቀል መፍትሔዎች የአየር ንብረት ጥበቃን ማረጋገጥ እንደሚችሉ ማረጋገጫ ሆኗል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና አምባሳደሮች የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ልማት እንቅስቃሴ ለአካባቢ ጥበቃ አርአያ የሚሆን ዓለም አቀፍ ሞዴል ሲሉ አድንቀውታል።   ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን ከመጠቀም፣የካርቦን ልቀትን ከመቀነስ እና ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መስፋፋት ጋር አጣጥማ የምታካሂደው እንቅስቃሴ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ እውቅና እንድታገኝ አስችሏታል።
ረብጣ ገንዘብ ከወጣባቸው ዝውውሮች እስከ አነጋጋሪ የህግ ለውጦች ፡ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲሱ የውድድር ዓመት ምን ይዞ መጣ?
Aug 21, 2026 336
በሙሴ መለሰ የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያን በጉጉት የሚጠብቀው የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ዛሬ በይፋ ይጀምራል። የዘንድሮው የውድድር ዘመን በሰኔ እና ሐምሌ ወራት የተካሄደውን የ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ተከትሎ፣ ለተጫዋቾች በቂ የእረፍት ጊዜ ለመስጠት ሲባል ከተለመደው አንድ ሳምንት ዘግይቶ እንዲጀምር ተደርጓል። የመክፈቻው ጨዋታ በኢምሬትስ ስታዲየም የባለፈው የውድድር ዘመን ሻምፒዮን አርሰናል እና ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ሊጉ በተመለሰው ኮቨንትሪ ሲቲ መካከል ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኤምሬትስ ስታዲየም ይካሄዳል። ይህ አዲስ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት በክረምቱ የተጫዋቾች ዝውውር መስኮት ላይ የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች ከፍተኛ ተሳትፎ አድርገዋል። እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት፣ የሊጉ ክለቦች ለተጫዋቾች ዝውውር ብቻ ከ2.14 ቢሊዮን ፓውንድ በላይ ወጪ አድርገዋል። ይህ የወጪ መጠን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከሌሎች የአውሮፓ አራት ታላላቅ ሊጎች (ስፔን፣ ጣልያን ጀርመንና ፈረንሳይ) በጥምረት ካወጡት የገንዘብ መጠን በላይ ሆኗል። ሞርጋን ሮጀርስ ከአስቶን ቪላ ወደ ቼልሲ በ117 ሚሊዮን ፓውንድ በመዘዋወር የክረምቱ ውዱ ተጫዋች መሆን ችሏል። ኤሊዮት አንደርሰን ከኖቲንግሃም ፎረስት ወደ ማንቸስተር ሲቲ በ116 ሚሊዮን ፓውንድ አምርቷል። በተጨማሪም ሳንድሮ ቶናሊ ከኒውካስል ወደ ቶተንሃም በ100 ሚሊዮን ፓውንድ፣ እንዲሁም ብሩኖ ጉማሬሽ ከኒውካስል ዩናይትድ ወደ አርሰናል በ75 ሚሊዮን ፓውንድ መዘዋወራቸው የክረምቱን የዝውውር ገበያ ከሚጠቀሱ ዝውውሮች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ከዝውውር ወጪው ባሻገር፣ የዘንድሮው የውድድር ዘመን በአዳዲስ አሰልጣኞች የታጀበ ሆኗል። በሊጉ ታሪክ ከፍተኛው በተባለ ደረጃ ዘጠኝ ክለቦች ውድድሩን በአዲስ አሰልጣኞች ይጀምራሉ። ፔፕ ጋርዲዮላ ማንቸስተር ሲቲን በገዛ ፈቃዱ መልቀቁን ተከትሎ የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አሁን ላይ በሊጉ ረጅም ጊዜ (ሰባት ዓመታት) የቆየው አሰልጣኝ ሆኗል። የቼልሲው ዣቢ አሎንሶ፣ የማንቸስተር ሲቲው ኤንዞ ማሬስካ እና የሊቨርፑሉ አንዶኒ ኢራኦላ ከአዳዲሶቹ አሰልጣኞች መካከል ይጠቀሳሉ። ማይክል ካሪክ በማንቸስተር ዩናይትድ እንዲሁም ሮቤርቶ ዴ ዜርቢ በቶተንሃም ሆትስፐርስ የመጀመሪያ ሙሉ የውድድር ዓመታቸውን ይጀምራሉ። የሊጉ የተሳታፊዎች ስብጥርን በተመለከተ፣ ኮቨንትሪ ሲቲ ከ25 ዓመታት በኋላ ከሃል ሲቲ እና ኢፕስዊች ታውን ጋር በመሆን ከታችኛው ሊግ አድገው ሊጉን ተቀላቅለዋል። በተቃራኒው ዌስትሃም ዩናይትድ፣ በርንሌይ እና ዎልቨርሃምፕተን ዋንደረርስ ባለፈው የውድድር ዘመን መውረዳቸው የሚታወስ ነው። በተጨማሪም የእንግሊዝ ክለቦች ባለፈው ዓመት በአውሮፓ ባሳዩት አስደናቂ ብቃት ምክንያት፣ በዚህ የውድድር ዘመን ክብረ ወሰን የሆነ ዘጠኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በአውሮፓ ውድድሮች ላይ ይሳተፋሉ። አርሰናል፣ አስቶንቪላ፣ ሊቨርፑል፣ ማንቸስተር ሲቲ እና ማንቸስተር ዩናይትድ በሻምፒዮንስ ሊግ የሚወዳደሩ ሲሆን፣ በርንማውዝ፣ ሰንደርላንድ እና ክሪስታል ፓላስ በዩሮፓ ሊግ እንዲሁም ብራይተን በኮንፈረንስ ሊግ አገራቸውን ይወክላሉ። የሊጉ አስተዳደር የክለቦችን የፋይናንስ ወጪ የሚቆጣጠር አዲስ የወጪ ገደብ (Squad Cost Ratio) መመሪያን ተግባራዊ አድርጓል። በዚህም መሠረት ክለቦች ለተጫዋቾች ደሞዝ እና ለዝውውር የሚያወጡት ጠቅላላ ወጪ ከገቢያቸው 85 በመቶ እንዳይበልጥ ተወስኗል። ህጉን የሚጥሱ ክለቦችም የነጥብ ቅነሳ ቅጣት ይገጥማቸዋል። የጨዋታ ፍጥነትን ለመጨመርና ሰዓት ማባከንን ለመግታት በርካታ አዳዲስ የዳኝነት ህጎች በይፋ ስራ ላይ ይውላሉ። በእጅ ውርወራ (Throw-in) እና በመልስ ምት (Goal-kick) ላይ ሰዓት ለሚያባክኑ ተጫዋቾች ዳኛው አምስት ሴኮንድ የሚቆጥር ሲሆን፣ ጊዜ ካለፈ እጅ ውርወራው ለተቃራኒ ቡድን ይሰጣል፤ የመልስ ምት ላይ ከሆነ ደግሞ የተቃራኒ ቡድን የማዕዘን ምት ያገኛል። ሌላው ሰዓት ማባከንን ለመቆጣጠር የወጣው ህግ ተጫዋቾች ታክመው ከወጡ በኋላ ወደ ሜዳ ለመመለስ ቢያንስ አንድ ደቂቃ ውጭ እንዲጠብቁ የሚያስገድደው ደንብ ነው። በተጨማሪም ተጫዋቾች በሚቀየሩበት ወቅት ከሜዳ ለመውጣት የ10 ሴከንድ ገደብ የተጣለባቸው ሲሆን፣ ይሁንና ጊዜው ካለፈ ተቀያሪው መግባት የሚችለው ጨዋታው በሚቀጥለው ጊዜ ሲቆም ብቻ ይሆናል። በዚህ የውድድር ዘመን የቪዲዮ ረዳት ዳኛ (VAR) ውሳኔዎችን ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ ትልቅ ማሻሻያ ተደርጓል። አንድ ተጫዋች በሁለተኛ ቢጫ ካርድ ከሜዳ ሲሰናበት አጠራጣሪ ከሆነ ቫር ጣልቃ የመግባት ስልጣን ተሰጥቶታል፤ እንዲሁም በጨዋታ ወቅት በቫር እና በሜዳ ላይ ዳኛው መካከል የሚደረጉ የድምፅ ውይይቶች በሊጉ የጨዋታ ማዕከል በኩል ለደጋፊዎች በቀጥታ ይፋ ይደረጋሉ። በአጠቃላይ፣ የዘንድሮው የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ከአዳዲስ የህግ ለውጦች፣ ከከፍተኛ የዝውውር ወጪዎች እና አዳዲስ የአሰልጣኞች ሹመት ጋር ተያይዞ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረትን ስቧል። አርሰናል የዋንጫ ክብሩን ለማስጠበቅ፣ ማንቸስተር ሲቲ ያለ ፔፕ ጋርዲዮላ አዲስ ምዕራፍ ለመጀመር፣ እንዲሁም አዳዲስ አሰልጣኞችና ክለቦች ህልማቸውን ለማሳካት የሚያደርጉት ፍልሚያ የእግር ኳስ አፍቃሪያን እስከ ግንቦት ወር መጨረሻ ድረስ የሚዘልቅ አስደሳች እና አጓጊ የእግር ኳስ ጊዜን እንደሚያሳልፉ አያጠራጥርም።
ቡሄ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ምስረታ ታሪካዊ ቁርኝት
Aug 19, 2026 544
በሙሴ መለሰ ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን የቡሄ በዓል በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ባለበት በዚህ ዕለት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አጀማመሩንና ምስረታውን ከዚህ በዓል ጋር ያለውን የጠበቀ ትስስር ወደ ኋላ መለስ ብሎ የሚታወስበት ነው። የክለቡ ምስረታና የቡሄ በዓል (የሆያ ሆዬ ጨዋታ) ቀጥተኛና የማይነጠል ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፣ ክለቡ በመስረታው ወቅት የነበረበትን የፋይናንስ እጥረት ቀርፎ የመጀመሪያውን ማሊያ ለመግዛት የበቃው በዚህ ዕለት በተሰበሰበ የሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ነበር። የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን መጀመሪያ ሲጠነሰስ በጆርጅ ዱካስና በአየለ አትናሽ አማካኝነት የነበረ ቢሆንም፣ ክለቡን በይፋ አደራጅቶ ለማቋቋም ግን የግድ የፋይናንስ አቅም ወይም ገንዘብ ያስፈልግ ነበር። ሆኖም ግን በሃገር ፍቅር ስሜት የተነሱት ዘጠኙ ወጣቶች ማለትም አየለ አትናሽ፣ ጆርጅ ዱካስ፣ ዮሐንስ ጥላሁን፣ ገብረመድህን ተፈሪ፣ ተፈራ ገብረእግዚአብሔር፣ ዓለማየሁ እጅጉ፣ መኮንን ደምሴ፣ አስፋው ያዕቆብ እና ክልቱ አያኖ ክለቡን በሚመሰርቱበት ወቅት ቤሳ ቤስቲን እንኳ ኪሳቸው ውስጥ ስላልነበራቸው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ተሰብስበው በሰፊው ተወያዩ። በዚህ የውይይት ወቅት ነው ገንዘብ ለማግኘትና የክለቡን መመስረት እውን ለማድረግ የቡሄ ቀን እጅግ መልካምና ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን የተረዱት። ዘጠኙ ወጣቶች በአንድ ድምፅ ተስማምተው በታሪካዊው የቡሄ ዕለት ማለትም ነሐሴ 13 ቀን 1927 ዓ.ም. በጋራ በመሆን ቡሄ ጨፍረው (ሆያ ሆዬ ብለው) በሚያገኙት ማናቸውም ነገር የክለቡን የመጀመሪያ ማሊያ ለመግዛት ቁርጥ የሆነ ውሳኔ ላይ ደረሱ። በዚያን ጊዜ የነበረው የባህል ልማድ አሁን ካለው የተለየ በመሆኑ፣ ቡሄ ሲጨፈር የሚሰጠው ጥሬ ገንዘብ ሳይሆን ሙልሙል ዳቦ ነበር። በመሆኑም ዘጠኙ ተጫዋቾችና መስራቾች ቀደም ሲል ከሚጨፍሩበትና ለምደውት ከነበረው አካባቢ ራቅ ብለው በመንቀሳቀስ በየቤቱ በር እያንኳኩ በደመቀ ሁኔታ ጨፈሩ፤ በዚህም ጥረታቸው በርካታ ቁጥር ያለው የሙልሙል ዳቦ በአንድነት ማሰባሰብ ቻሉ ታሪካዊውን ስራ ሰሩ። ይሁን እንጂ የተሰበሰበውን ይህንን በርካታ ዳቦ ወደ ጥሬ ገንዘብ ለመቀየር አዲስ አበባ ውስጥ ወደሚገኘው ሰራተኛ ሰፈር ለሚገኙ ወዛደሮች ለመሸጥ ዳቦውን በከረጢት ይዘው ጉዟቸውን ጀመሩ። በዚህ የጉዞ መስመር ላይ ሳሉ ግን ያልተጠበቀ ፈተና ገጠማቸው፤ በመንገድ ላይ ያገኟቸው “ዱርዬዎች” ከተሰበሰበው ዳቦ ላይ የተወሰነውን ነጠቋቸው። ወጣቶቹ ተስፋ ሳይቆርጡ ጉዟቸውን በመቀጠል የተረፈውን ዳቦ ለሰራተኛ ሰፈሩ ወዛደሮች በመሸጥ ማሊያ መግዣ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ በእጃቸው አስገቡ። ከዳቦው ሽያጭ የተገኘችው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን በወቅቱ መገበያያ በትክክል ሁለት ጠገራ ብር ነበረች። የክለባችው የመጀመሪያ መለያ ቡናና ነጭ ነበር። ቡናና ነጭ መሊያን የገዙት ግን ፈልገው አልነበረም በቂ ገንዘብ ስላልነበራቸው በሁለት ጠገራ ብር ከፒያሳ «ግሪካዊ አውግስታስ ዱስ» ከተባለ ሱቅ በርካሽ ስላገኙት ነበር። ይህ በቡሄ ዕለት የተጀመረው ታሪካዊ የማሊያ ግዢ በኋላ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በታህሣሥ ወር 1928 ዓ.ም. በይፋ ተመሠረተ። ክለቡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለብ በመሆን ታሪካዊ ማዕረግንና ቀዳሚነትን ተቀዳጀ። በ1928 ዓ.ም. በይፋ የተመሰረተው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በታሪኩ የመጀመሪያውን የሜዳ ጨዋታ ያደረገው ከ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ነበር። በዚሁ ታሪካዊ የመጀመሪያ ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። በዕለቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠንካራ ተፎካካሪ ከነበረው የ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ለመጫወት ወደ ሜዳ ሲያመራ፣ አስቀድመው ከተመረጡትና ቡድኑን ካደራጁት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ባልታወቀ ምክንያት ሳይመጣ ቀረ። በዚህ ድንገተኛ መቅረት ምክንያት ቡድኑ በሰው ጎደሎ ለመጫወት በተገደደበት ወሳኝ ሰዓት፣ መስራቾቹ በሜዳው አቅራቢያ መንገድ ላይ ሲጫወት ያገኙትን አንድ ታዳጊ ወጣት ተመለከቱ። ይህ ታዳጊ በወቅቱ ገና የ14 ዓመት ዕድሜ የነበረውና በኋላ ላይ የኢትዮጵያ ስፖርት ባልደረባ የሆነው ይድነቃቸው ተሰማ ነበር። ወጣቶቹም ያለ ምንም ቅድመ ዝግጅት ቡድኑን እንዲሞላ ድንገት ጋበዙት፤ እርሱም የቀረበለትን ጥሪ በደስታ ተቀብሎ በአጋጣሚ ወደ ሜዳ ገባ። ያለ ምንም ልምምድና ዝግጅት በድንገት የተሰለፈው ይድነቃቸው ተሰማ፣ በሜዳ ላይ ያሳየው አስደናቂ ችሎታና ቅልጥፍና ሁሉንም ያስገረመ ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ታሪካዊ ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ፣ ለክለቡ የመጀመሪያውን ድል ያስገኙትን ሁለቱንም ታሪካዊ የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ይኸው መንገድ ላይ ተገኝቶ በድንገት የተሰለፈው ታዳጊ ይድነቃቸው ነበር። ይህ ብቃት ገና በታዳጊነቱ በክለቡ ውስጥ ያለውን የማይተካ ቦታ ከማረጋገጡም በላይ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን የድል ጉዞ በደመቀ ሁኔታ እንዲጀመር አድርጓል። ቡሄ በዓል እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ያላቸው ታሪካዊ ቁርኝት የክለቡን ጥልቅ ህዝባዊና ባህላዊ መሰረት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቀዳሚ ፋና ወጊ የሆነው ይህ ታላቅ ክለብ፣ በታሪካዊቷ የነሐሴ 13 ቀን የቡሄ ዕለት የመስራቾቹ የ"ሆያ ሆዬ" ጨዋታና ከተሰበሰበው ሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ባገኟት ሁለት ጠገራ ብር የመጀመሪያውን ቡኒና ነጭ ማሊያ መግዛቱ፣ ክለቡ ከህዝብ ማህፀን የወጣ የህዝብ ሀብት መሆኑን ያረጋግጣል። ይህ ከባህልና ከትውፊት ጋር የተቆራኘ አስደናቂ አጀማመር፣ ከጊዜ በኋላ በ1928 ዓ.ም. ለይፋዊ ምስረታው በር ከፋች ከመሆኑም በላይ፣ በታሪካዊው የመጀመሪያ ጨዋታ ላይ እንደ ይድነቃቸው ተሰማ ያሉ የአፍሪካ እግር ኳስ ታላላቅ መሪዎችና ድንቅ ተሰጥኦዎች እንዲፈጠሩ መሰረት የጣለ የኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ነው።
ቡሄ የትውልድ ወጋገን፤ የማኅበራዊ ትስስር አምድ
Aug 19, 2026 446
ቡሄ በወርሃ ነሐሴ በ13ኛው ቀን ህፃናት ሆያ…. ሆዬ….! ሆ…. በሚል ዜማና ጅራፍ እያጮሁ የሚያከብሩት፤ እናቶች ለህፃናቱ ሙል ሙል ዳቦ በመስጠት እንኳን አደረሳችሁ እያሉ በድምቀት የሚያከብሩት በዓል ነው። ቡሄ ትርጓሜውም ብርሃን፣ብራ፣ ወጋግን ማለት ሲሆን ከጨለማ ወደ ብርሃን የመሸጋገሪያ የተስፋ ምልክት ነው። በሀይማኖታዊ አንድምታው በዓሉ የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ ብርሃን በደብረ ታቦር ተራራ ላይ መገለጡ የሚታሰብበት ነው፤ በዚህም ደብረ ታቦር ይባላል፡፡ የክረምቱ ጭጋግ ተገፎ የብርሃን ወጋገን የሚታይበት ሕፃናትና ወጣቶች በየቤቱ እየዞሩ «ሆያ ሆዬ» በማለት በረከትና ምርቃት የሚያፍሱበት የደስታና የፍቅር መግለጫ ነው። ህፃናትና ወጣቶች በየዕድሜያቸው ጅራፍ እያጮሁ በሕብረ ዝማሬዎች እየደመቁ በአብሮነት እና በደስታ የሚያከብሩት ትውፊታዊ በዓል ነው ቡሄ። የወጣቶችን ጉርብትና እና ማኅበራዊ ትስስር የሚያጎለብት እሴት ነው፤ በአከባበሩ ወቅት የሚንጸባረቀው የመረዳዳትና ያለውን የመካፈል ባህል ፋይዳውን ከትውልድ ወደ ትውልድ ማሸጋገር ያስችላል። የቡሄ በዓል ባህላዊ እሴቶችን በመጠበቅ፣ ትውልድን በማቀራረብ እና ማኅበራዊ ትስስርን ይበልጥ በሚያጠናክር ተምሳሌትነቱ እልፍ ነው። በአዲስ አበባ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከፍተኛ የቅርስ ጥናት ተመራማሪ መምህር መክብብ ገብረማሪያም ለኢዜአ እንዳሉት፤ የቡሄ በዓል የብርሃን ዘመን መምጣቱን የተስፋ ጎህ መቅደዱን ማብሰሪያ ነው፡፡ ቡሄ ከጨለማ ወደ ብርሃን ሽግግር መምጣቱን የሚያበስር በታዳጊዎች የሚዘከር የፍቅር፣ የአንድነትና የበረከት መገለጫና ተስፋ መሆኑን ያነሳሉ፡፡ ታዳጊዎችና ወጣቶች በበዓሉ ወቅት የሚያዜሙት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሸጋገር የመጣው የ«ሆያ ሆዬ» ሕብረ ዜማ ለጋራ ትርክት ግንባታ ገንቢ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል። ቡሄ የትውልድ ወጋገን፤ የማኅበራዊ ትስስር አምድ በመሆኑ ማኅበራዊ ትስስርና የጋራ ዕሴቶችን ማጠናከር ያስችላል ብለዋል።   ታዳጊው በሱፈቃድ አስሜ ቡሄ ከጓደኞቹ እና ከወዳጅ ዘመዶቹ ጋር ፍቅርንና አብሮነትን ይበልጥ የሚያጠናክርበት የደስታና የተስፋ በዓል መሆኑን ይናገራል፡፡ ቡሄ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠብቀውና ቀጣይ ሕይወቱን በአዲስ መንፈስ ለመምራት አቅም የሚፈጥርለት የብሩህ ዘመናትን ማለሚያ መሆኑን ይገልፃል። ቡሄ ከታላላቆቹ የወረሰው ከእኩዮቹ ጋር በፍቅርና በደስታ የሚያከብረው ነገን በተስፋ የሚያይበት ውብ በዓል እንደሆነ የሚናገረው ደግሞ ታዳጊው በረከት ምናለ ነው፡፡   የተጣሉ ጓደኛሞች እርቅ የሚያወርዱበት በዓል በመሆኑ ለትውልድ አንድነት እና አብሮነትን በማስተማር ረገድ ትልቅ ድርሻ አለውም ብሏል። ወጣት ያብስራ ጸጋዬ በበኩሉ ቡሄ በዓመት አንድ ጊዜ የሚመጣ፤ ተራርቀው ከሚኖሩ የተለያዩ አካባቢ እኩዮቹ ጋር በአንድነት የሚያከብሩት በዓል መሆኑን ይናገራል፡፡   ከሁሉም ዓይነት ሕብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ታዳጊዎች የሚሰባሰቡበት፤ ሕብረ ብሔራዊነትን የሚያጠናክር የጋራ በዓል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ በኃይሉ ሞገስ ናቸው።      
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ-የቀይ ባሕር ደህንነትና የቀጣናዊ መረጋጋት ዋስትና!
Aug 23, 2026 370
ኢትዮጵያ-የቀይ ባሕር ደህንነትና የቀጣናዊ መረጋጋት ዋስትና! የቀይ ባሕር ቀጣና በዓለም አቀፍ የንግድ ዝውውር፣ በጂኦፖለቲካዊ ትስስር እና በባሕር ላይ ደህንነት ረገድ ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ቦታ የሚይዝ ቀጣና ነው።ሆኖም በአሁኑ ወቅት አካባቢው የተለያዩ ፍላጎት ያላቸው ኃይሎች መራኮቻ፣የባሕር ላይ ወንበዴነት፣ የሕገ-ወጥ ንግድና የሽብር ስጋቶች የተጋረጡበት በመሆኑ፣ዘላቂ ሰላምና ደህንነቱን ለማረጋገጥ ጠንካራና አስተማማኝ አቅም ያለው ቀጣናዊ አጋር ያስፈልገዋል።ኢትዮጵያ በ130 ሚሊዮን ሕዝቧ፣ በገነባችው ግዙፍ ኢኮኖሚ፣በጠንካራ የመከላከያና የባሕር ኃይል አቅሟ እንዲሁም ቅድሚያ ለጎረቤት በሚለው የመደመር ዲፕሎማሲያዊ መርህዋ የቀይ ባሕርና የመላው ቀጣናው ደህንነት ዋስትና ሆና ወጥታለች። ኢትዮጵያ ከራሷ ባለፈ ሀገራት ግጭት ሲያጋጥማቸው፣ለችግር ሲጋለጡ ቀድማ የምትደርስ፣ ሰላምን በማስከበርና መረጋጋትን በመፍጠር በጽኑ መሠረት እንዲቀጥሉ በማስቻል የምትታወቅ ሀገር ናት።በ1950ዎቹ የኮሪያ ጦርነት ወቅት የተባበሩት መንግሥታትን ጥሪ በመቀበል ከ3 ሺህ 500 በላይ ወታደሮቿን በመላክ በዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ የፈጸመችው ገድል የቃኘው ሻለቃ በጦር ሜዳ ላይ ያሳየው ጀግንነትና የከፈለው መስዋዕትነት እስከ ዛሬ በዓለምና በደቡብ ኮሪያ ሕዝብ ዘንድ በከፍተኛ አክብሮት ይታወሳል። ይህ የሰላም ማስከበር ተሳትፎ ኢትዮጵያ አፍሪካን ጭምር ያኮራችበት ነበር። ከዚያ በኋላም በኮንጎ፣በሩዋንዳ፣ በላይቤሪያ፣ በቡሩንዲ፣ በዳርፉር፣ በአብዬ እና በደቡብ ሱዳን ያበረከተችው አስተዋጽኦ በአፍሪካ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ወደር የለሽ ሀገር ያደርጋታል። በሶማሊያ ደግሞ ኢትዮጵያ የደም ዋጋ ከፍላ ሀገሪቱን በአሸባሪዎች ከመበታተንና ከመፍረስ ታድጋለች። የአልሸባብን ስጋት በመግታትና የሶማሊያን መንግሥት በመደገፍ ለቀጣናው ደህንነት የማይተካ ሚና ተጫውታለች። ዛሬም በተባበሩት መንግሥታትና በአፍሪካ ሕብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ዋነኛዋ ሀገር ሆና ቀጥላለች።ይህ የካበተ ልምድ ኢትዮጵያን የቀጣናው የደህንነት ዋስትና እንድትሆን አድርጓታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር እሳቤያቸው እንዳመላከቱት፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት ከሁሉም የውጭ ግንኙነቶች ቅድሚያ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነው። መደመር ከአጎራባች ሀገራት ጋር የምናደርገው ግንኙነት ብሔራዊ ጥቅምን በአብዛኛው በጋራ ጥቅም ላይ ተመሥርቶ የሚመራ መሆን ይኖርበታል የሚል የጸና አቋም ያራምዳል። ዕጣ ፈንታችን የተሳሰረ ስለሆነ የጋራ ጥቅሞቻችንን መሠረት ያደረገ ትብብርና መተጋገዝ ያስፈልገናል የሚለው መርህም ኢትዮጵያ አሁን እየተራመደችበት ያለው የገቢር ነበብ ዲፕሎማሲ መገለጫ ነው። ኢትዮጵያ በመደመር እያንዳንዱ የልማት እርምጃዋ፣ ቀጣናዊ መሻቷ ጎረቤቶቿን የሚያግዝና ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ጎረቤቶቿ ለችግር በተዳረጉ ጊዜም ቀድማ ደራሽ ናት። የሰላማቸው አምባ፣ የሀዘናቸው አጽናኝ ናት። ለአብነትም ሱዳን ከባድ ቀውስ ውስጥ በገባች ጊዜ 15 ሚሊዮን ዶላር በመደገፍ የችግር ጊዜ የአብሮነት መርሗን በተግባር አሳይታለች። በሺዎች የሚቆጠሩ ሱዳናውያን ስደተኞችን በሯን ከፍታ ተቀብላ በማስጠለል ሰብዓዊ ኃላፊነቷን እየተወጣች ነው።ይህ ድርጊት ኢትዮጵያ የጎረቤቶቿ ሕመም የሚያማት፣ እንደ ዋርካ ሆና የምታሳርፍ፣ ለጋራ ጥቅም ቀድማ የምትሰለፍ መሆኗን በግልጽ ያሳያል። ኢትዮጵያ ወንዞቿና ጅረቶቿ የቀጣናውን ሀገራት የሚያለሙ፣ ለም አፈሯ ምግብ የሆናቸው ሀገር መሆኗም የማይታበል ሐቅ ነው። የመደመር መንግሥት ይህንን ተፈጥሯዊ ሚዛን በእሴት የጨመረ የትብብር ድልድይ አጽንቷል። በዓባይ ወንዝ ላይ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በመገንባት የቀጣናው የብርሃን ምንጭ እንዲሆን አድርጎታል። ግድቡ ለሱዳን፣ ለጅቡቲና ለኬንያ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር የጋራ ልማትን እውን እያደረገ ነው። ኢትዮጵያ ሌሎች የኃይል ማመንጫዎችን በመገደብ የቀጣናውን የኃይል ዋስትና የበለጠ ለማጠናከር ቁርጠኝነቷን በተግባር እያሳየች ትገኛለች። ይህ በመደመር መንግሥት የሚተገበር ራዕይ ኢትዮጵያ የቀጣናው የጋራ የኢነርጂ ደህንነት ምሰሶ መሆኗን ያረጋግጣል። የኢኮኖሚ ጥንካሬ፣ የምግብ ሉዓላዊነትና የቀጣናው ተስፋ የመደመር መንግሥት በተከተለው የጠራ እሳቤ ኢትዮጵያ ግዙፍ ኢኮኖሚ እየገነባች ነው። ይህም ትሩፋቱ ለቀጣናው ሀገራት ጭምር እየተትረፈረፈ ነው። በመሠረተ ልማት፣ በኢነርጂ፣ በኢንዱስትሪና በግብርና ዘርፍ የተከናወኑት ስኬቶች ሀገሪቱ የምግብ ዋስትናን በቀጣና ደረጃ ለማረጋገጥ ምሳሌ አድርጓታል። የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ በጀመረችው የስንዴ ልማት ኢኒሼቲቭ እመርታዊ ስኬት አስመዝግባለች። ለዓመታት በድርቅና በሌሎች ችግሮች የሚያጋጥማትን ሰብዓዊ ድጋፍ በእርዳታ ስትሸፍን የነበረችውና ለፍጆታ የሚሆን ስንዴንም ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ በማውጣት ስታስገባ የቆየችው ኢትዮጵያ፣ ዛሬ ላይ በሚሊዮን ሄክታር የሚቆጠር ስንዴን በበጋ መስኖና በክረምት በማልማት በዓመት 33 ሚሊዮን ቶን ስንዴ የምታመርት ሀገር ሆናለች። በአፍሪካ ቀዳሚዋ ስንዴ አምራች ሀገር፣ ከውጭ የምታስገባውን ስንዴ በራሷ ምርት የተካች ሀገር፣ ለሌሎች ጎረቤት ሀገራት ስንዴ የምትልክ ሀገር በመሆንም እየተጠቀሰች ነው። የምግብ ሉዓላዊነቷን በማረጋገጥ ጉዞዋ በመስኖ የሚለሙ መሬቶችን በከፍተኛ ሁኔታ በማስፋፋት፣ የክላስተር እርሻን በማጠናከር ኢትዮጵያ ከተረጂነት ራሷን ወደመቻል ተሸጋግራለች። ይህ የኢትዮጵያ ስኬት ለቀጣናው የምግብ ዋስትና መረጋገጥ ተምሳሌት ሆኗል። ባለፉት ስምንት ዓመታት ድርቅን መቋቋም የሚችል የግብርና ሥርዓት በመገንባትና በረሃዎቿን በማልማት ምርትና ምርታማነትን አሳድጋለች። በተለይም በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ለተደጋጋሚ የድርቅ አደጋ ተጋላጭ ለሆነው ቀጣና ተግባራዊ ምሳሌን በአረንጓዴ አሻራ አሳይታለች። ባለፉት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ሀገርን አረንጓዴ አልብሳለች። አረንጓዴ አሻራዋ ድንበር ተሻግሮ የቀጣናው የተስፋ ምንጭም ሆኗል። የቀይ ባሕር ባለቤትነት ታሪካዊ መብትና የቀጣናው ደህንነት ኢትዮጵያ ለሺህ ዓመታት ቀይ ባሕርን ተፈጥሯዊ ወሰኗ በማድረግ የአዱሊስ፣ የምጽዋና የአሰብ ወደቦችን ስታስተዳድርና የንግድ ዝውውሩን ስታስጠብቅ የቆየች ሀገር ናት። በታሪካዊ አጋጣሚዎች ምክንያት ከባሕር ተገልላ የቆየች ቢሆንም፣ ለ130 ሚሊዮን ሕዝቧ፣ ለግዙፍ ኢኮኖሚዋ እና ለቀጣናው ደህንነት ሲባል የባሕር በር ማግኘት የህልውና ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ የባሕር ኃይሏን ዳግም በጥንካሬ በማደራጀት ስትራቴጂካዊ እርምጃ ወስዳለች። ይህ ዝግጁነት የቀይ ባሕርን የንግድ መስመር ከባሕር ወንበዴዎች ለመጠበቅ፣ የሕገ-ወጥ የሰዎችና የጦር መሣሪያ ዝውውርን እንዲሁም የሽብር እንቅስቃሴዎችን ከሥር ለማምከን የሚረዳ ነው። ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነቷን በሰላማዊ መንገድ፣ በዲፕሎማሲና በጋራ ጥቅም መርህ ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የመላው ቀጣናው አሸናፊነት ማረጋገጫ ይሆናል። ማጠቃለያ ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሰላም፣ ልማትና መረጋጋት ቀዳሚ ሚናዋን ስታበረክት የቆየች የምስራቅ አፍሪካ ምሰሶ ናት።የኢትዮጵያ አቅምና ዝግጁነት ለቀይ ባሕር ቀጣና ደህንነት ዋስትና የሚሰጥ እንጂ ማንንም ሀገር የሚጎዳ አይደለም። በጋራ ጥቅም እና በቅድሚያ ለጎረቤት መርህ የሚሳካው የኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባሕር መመለስ ለቀጣናው የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የሎጂስቲክስ ቅልጥፍና እና ለጋራ ደህንነት መረጋገጥ ወሳኝ ድርሻ ይጫወታል። ዛሬም በመደመር እሳቤ፣ በጠንካራ ኢኮኖሚ፣ በጠንካራ የመከላከያ ኃይልና በቅድሚያ ለጎረቤት በሚሰጥ ጠንካራ ዲፕሎማሲ የቀጣናውን የተሻለ ነገ እየገነባች ነው። በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ያሳየችውን የጋራ ተጠቃሚነት መርህ የቀይ ባህር ባለቤትነት መብቷን በማሳካትም ትደግመዋለች። የልማት ተስፋና የቀጣናው የደህንነት ዋስትናነቷን በገቢር ነበብነት ታረጋግጣለች።
ከህዳሴ ግድብ እስከ ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ - የኢትዮጵያ አህጉራዊ የመሰረተ ልማት መሪነት
Aug 21, 2026 976
(በሙሴ መለሰ) መሰረተ ልማት የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ማዕዘን ከሆኑ ቁልፍ ዘርፎች መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢትዮጵያ የነገ ብልጽግናዋን እውን ለማድረግና የዜጎቿን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተፋጠነ መልኩ እየተገበረቻቸው የሚገኙት ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ቁልፍ ሚና አላቸው ። በመንገድ፣ በባቡር፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ የኮሪደር ልማት እና ሌሎች ግንባታዎች ላይ እያፈሰሰች ያለው መዋዕለ ንዋይ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን የሚመጥን የኢኮኖሚ እድገት እና የአኗኗር ዘይቤን በመፍጠር ረገድ ያላቸው አስተዋጽኦም ቀላል አይደለም። ግዙፉ ፕሮጀክቶቿ መካከልም በጳጉሜን ወር 2017 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለአፍሪካ የኢነርጂ ትስስር ውጥን ትልቅ የምስራች ሆኖ መጥቷል። የጎረቤት ሀገራት ከግድቡ የሚያገኙት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር ያስችላል። በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙ የሀገራት መሪዎች ባደረጉት ንግግርም በአጽንኦት ያረጋገጡት የህዳሴ ግድብ የአፍሪካ የራስን የመቻል ምልክት እና የኢትዮጵያን አይበገሬነት ተምሳሌትነት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህዳሴ ግድብ ምርቃት ወቅት የተለያዩ ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እንደሚጀመር ይፋ አድርገዋል። የኒውክሌር ኃይል ማበልጸጊያ፣ የጋዝ ፋብሪካ ማስመረቅ፣ የነዳጅ ማጣሪያ እውን ማድረግ፣ በአፍሪካ ግዙፉ አየር ማረፊያ የሆነውን የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ መጀመር፣ ሁለተኛውን የጋዝ ፋብሪካ ግንባታ ማስጀመር፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ማስጀመር እና የ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶች በመላው ሀገሪቱ ማስጀመር በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ የተደረጉ ፕሮጀክቶች/የጉባ ብስራቶች/ ናቸው። በሶማሌ ክልል የጋዝ ፋብሪካ የተመረቀ ሲሆን፣ በአፍሪካ ታሪክ በትልቅነቱ ቀዳሚ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛል። ይህ ግዙፍ የአየር ማረፊያ ፕሮጀክት የሀገሪቱን የሎጂስቲክስና የቱሪዝም አቅም ከመቀየር ባለፈ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ያላትን የአቪዬሽን መሪነት ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የሀገሪቱን የግብርና ምርታማነት በዘላቂነት ለመደገፍ ወሳኝ የሆነው የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ እና የ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ በየክልሎቹ ካሉ የከተማ ማዘመንና የኮሪደር ልማት ስራዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ ወደ ተግባር እየተሸጋገረ ይገኛል። በግንባታ ላይ የሚገኘው የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ግንባታም ለኢነርጂ አቅርቦት እድገት የበኩሉን ሚና የሚጫወት ሲሆን፣ ሀገሪቱ የጀመረችውን የአረንጓዴ ኢነርጂና የኢንዱስትሪ ልማት ጉዞ በከፍተኛ ደረጃ ያፋጥነዋል። እነዚህ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ሀገሪቱ በቅርቡ ከጀመረችው አጠቃላይ የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የገበያ መር ሥርዓት ጋር የተቆራኙ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች ተደርገው ይወሰዳሉ። የሀገር ውስጥ ምርታማነትንና የዜጎችን የኑሮ ጥራት ከመሰረቱ የሚያሻሽሉ ከመሆናቸውም በላይ፣ ሀገሪቱ በውጭ ዕርዳታና ብድር ላይ ከመደገፍ ወጥታ በሀገር ውስጥ እቅድና አቅም ላይ ተመስርታ የራሷን ዕድል የምትወስን አይበገሬነቷን በተግባር ያሳዩ የኩራት መገለጫዎች ናቸው። መንግሥት በነዳጅ፣ በጋዝ፣ በማዳበሪያ እና በ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ ላይ የጀመራቸው ግዙፍ ፕሮጀክቶች ቀደም ሲል የነበረውን የመንግሥትን ብቻ ፋይናንስ ጥገኝነት በመቀነስ፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ የግል ባለሀብቶችን (Private Sector) በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳትፉ አዳዲስ የአጋርነት ሞዴሎችን የፈጠሩ ናቸው። የተቀናጁ መሰረተ ልማቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለውን የንግድና የኢኮኖሚ ትስስር በማላቅ ቀጣናዊ ትብብርን ወደ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ በመሆናቸው፣ ኢትዮጵያ በአህጉራዊ ትስስርና በአፍሪካ የነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነቶች ውስጥ ያላትን ተወዳዳሪነትና ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድጉት አያጠራጥርም። በመሆኑም እነዚህን ስትራቴጂካዊ የካፒታል ፕሮጀክቶች ከተጀመሩት የከተማ ማዘመንና የኮሪደር ልማት ስራዎች ጋር መተሳሰር፣ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌትና የኢኮኖሚ ማዕከል አድርጎ ለመገንባት ለተቀመጠው የረጅም ጊዜ ሀገራዊ ራዕይ መሳካት አስተማማኝ ዋስትና ተደርገው ይወሰዳሉ። የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያዊያንን የእድገት መሻት ለማሳካት የሚያከናውነው የተቀናጀ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ነው። ለዚህ ስኬት ደግሞ ሁሉም ዜጋ እጅ ለእጅ ተያይዞ በጋራ መንቀሳቀስ ይኖርበታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገጽ 221 ላይ እንዳመለከቱት አይበገሬነት አንድ አካል ለብቻው የሚወጣው ጉዳይ አይደለም ። ከብዙዎች ጋር ተደምረን የጋራ ጉዳይ መሆኑን ተግባብተን በመደጋገፍና በመተባበር የምንወጣው ጉዳይ ነው።
የግብጽ እኩይ ሴራ የማይገታው የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት መብት
Aug 19, 2026 986
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች የምትገኘው እና የቀጣናው የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋት ዋና መሠረት ነች። የኢትዮጵያ፣ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የፖለቲካ ፍላጎት ሳይሆን ሀገራዊ ሕልውናንና ደህንነትን የማረጋገጥ፣ የልማትና ብልጽግናን ዕውን የማድረግ የትውልድ ጥያቄ ነው። ትልቅ አቅም ያላት ኢትዮጵያ በመልክዐ-ምድራዊ እስር ውስጥ እንድትቀር የሚደረገው ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍትሕን የሚቃረን አካሄድን ለማረም ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት የነበራት የባህር በር ባለቤትነት እና የማሪታይም መብት በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እየሰራች ነው። ይህ የኢትዮጵያ ፍትሐዊና የማይቀረው የሕልውና ጥያቄ በዓለም አቀፉ የባሕር ሕግ ኮንቬንሽን (UNCLOS) የተረጋገጠ እና በጋራ ተጠቃሚነት (Win-Win) መርሕ ላይ የተመሠረተ ቢሆንም፣ የግብጽ ፖሊሲ አውጪዎች ግን ይህንን የሕልውና ጥያቄ ለማክሸፍ የሴራ እና የከበባ ስትራቴጂያቸውን ለማስፈጸም እየሰሩ ይገኛሉ። የግብጽ ሴራ በዋናነት ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ለወደብ ኪራይ እንድታወጣ በማስገደድ፣ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት የሚወጣው ካፒታል እንዲሟጠጥ በማድረግ የሀገሪቱን የኢንዱስትሪያላይዜሽንና የልማት ዕድገት ለማቀጨጭ ያለመ የኢኮኖሚ ዘመቻ ነው። በተጨማሪም ግብጽ የቀይ ባሕርን ማሪታይም ቀጣና “የባሕር ዳርቻ ሀገራት ብቻ (Littoral States) ይዞታ" አድርጋ በመሳል፣ የኢትዮጵያን ታሪካዊና ሕጋዊ የመጠቀም መብት በመካድ ከማንኛውም የቀይ ባሕር የደህንነትና የኢኮኖሚ ስብስብ እንድትገለል እየሰራች ትገኛለች። ግብጽ ከኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርጋቸው ወታደራዊ ስምምነቶች በሰሜንና በምሥራቅ ድንበሮች አካባቢ አዲስ የደህንነት ስጋት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ ሀብቷንና ትኩረቷን ወደ የብስ ጥበቃ እንድታዞርና ለባህር ኃይል ግንባታ የምታውለውን አቅም እንድታበታትን የታለመ የከበባ ስልትም ነው። በዓለም አቀፍ የፋይናንስና የኢንቨስትመንት ተቋማት ዘንድ የምታደርገው የዲፕሎማሲ ጫና፣ ኢትዮጵያ ለወደብ እና ለትራንስፖርት ኮሪደሮች ልማት የሚሆን የውጭ ኢንቨስትመንት እንዳታገኝ እና የቀይ ባሕር አካባቢ የስጋት ቀጠና ተደርጎ እንዲቆጠር በማድረግ ኢንቨስተሮች እንዲሸሹ በማድረግ ላይ ናት። በጎረቤት ሀገራት ዘንድ የጥርጣሬ እና የስጋት ግንብ በመገንባት፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር የምታደርጋቸው ፍትሐዊና የጋራ ዕድገትን ያለሙ የወደብ ስምምነቶች የሉዓላዊነት መጣስ ተደርገው እንዲቆጠሩ የማስፈራራትና የሐሰት ትረካና ዘመቻ ታካሂዳለች። ግብጽ የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት ላይ አንድ ወጥ አቋም እንዳይዙ ለማድረግ ድርጅቶቹን የፖለቲካ ፍልሚያ መድረክ በማድረግ የቀጣናውን ተቋማዊ ትብብር የማደናቀፍ ተግባር እያከናወነች ይገኛል። የግብጽ ሚዲያዎች የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ የ130 ሚሊዮን ሕዝብ የረጅም ጊዜ ሕልውና እና የትውልድ ጥያቄ መሆኑ እየታወቀ ጠባብ የፖለቲካ አጀንዳ በማስመሰል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲይዝ የማድረግ ስራ ላይ ተጠምደዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና (AfCFTA) ውስጥ የምታደርገውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ፣ የወደብ ትራንዚት ወጪዋ ከፍተኛ ሆኖ እንዲቀጥል በማድረግ ምርቶቿ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ጫና ለመፍጠር ትሰራለች። የግብጽ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን ለዘለቄታው የመልክዐ-ምድር እስረኛ አድርጎ በማስቀረት፣ በምሥራቅ አፍሪካ የሚኖራትን ጂኦ-ፖለቲካዊና የኢኮኖሚ የበላይነት መግታት ነው። ሆኖም የግብጽ ሴራ የኢትዮጵያን የልማት መንገድ ሊያስቆመው አይችልም። ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በሕዝቦቿ የማይበገር ጽናትና ቁርጠኝነት እውን እንደሆነ ሁሉ፤ በቀይ ባህር ላይ ህጋዊና ፍትሃዊ መብትን የማረጋገጥ ጉዞም የቀጣናውን የታሪክ ሂደት የሚቀይር የማይቀለበስ ብሔራዊ የህልውና ጉዳይ ነው።
መደመር የደረመሠው የጠላት ካምፕና የባንዳዎች እሪታ
Aug 19, 2026 798
በምስራቅ አፍሪካና በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የካይሮ እጅ ሁልጊዜም ኢትዮጵያን ማዕከል ያደረጉ እኩይ ስትራቴጂዎችን በመተለም ይታወቃል። የዓባይ ወንዝ ዋነኛ ምንጭና የተፈጥሮ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያን ማዳከም፣ የውስጥ ግጭቶችን ማበረታት እና በቀይ ባሕር እንዲሁም በኤደን ባሕረ-ሰላጤ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍላጎት ማደናቀፍ የግብፅ የረጅም ጊዜ የውጭ ፖሊሲ መሠረት ሆኖ ቆይቷል። ግብፅ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በወታደራዊ ኃይል ኢትዮጵያን በግልጽ ወርራ ለመቆጣጠር ባደረገችው ሙከራ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1875 በጉንደት እንዲሁም 1876 በጉራዕ ጦርነቶች በኢትዮጵያ አሳፋሪ ሽንፈት አስተናግዳለች ። ከዚህ የቀጥታ ወታደራዊ ሽንፈት በኋላ ካይሮ ኢትዮጵያን በግልጽ ጦርነት ማንበርከክ እንደማትችል ተረድታ ወደ ተዘዋዋሪ የውስጥ ሴራና የእጅ-አዙር ጦርነት ተሸጋግራለች። ካይሮ ኢትዮጵያ ጠንካራና የበለፀገች ሀገር ሆና ከተነሳች በዓባይ ውሃ ላይ ያላትን አጠቃላይ የበላይነት እንደምታጣ ስለሚሰማት፣ የሀገሪቱን እድገት የማደናቀፍና በጂኦፖለቲካው መስክ ወደብ አልባ አድርጎ የመዝጋት ስትራቴጂን ለዘመናት ስትከተል ኖራለች። ይህም የታሪክ እውነታ ከትላንት እስከ ዛሬ በስውርና በግልጽ የሴራ መረቦች ተሸርቦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሲፈታተን የኖረ መራራ እውነት ነው። የቡትሮስ ብትሮስ ጋሊ የዲፕሎማሲ ሽፋን እና ኢትዮጵያን ወደብ የማሳጣት ሴራ በታሪክ አጋጣሚዎች እንደምናየው፣ በግብፅ የፖለቲካ ልሂቃን የታቀዱ ሴራዎች በዓለም አቀፍ መድረኮች እንዴት ተግባራዊ እንደሆኑ አንደኛው ማሳያ የቀድሞው ግብፃዊ ዲፕሎማት ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ አካሄድ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በ1970ዎቹ መጨረሻ በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራር በነበሩበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ በውስጥ ግጭት እንድትታመስና የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ ስጋት እንዳትሆን ከበስተጀርባ የዓመፅ ኃይሎችን የማጠናከር ስራ ሲሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ሃቅ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በውሃ ፖለቲካ ረገድ በሰጡት የታወቀ ንግግራቸው “ቀጣዩ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና የሚካሄደው ጦርነት በፖለቲካ ምክንያት ሳይሆን በውሃ ምክንያት የሚደረግ ይሆናል” በማለት ለቀጣናው ያሰቡ መስለው የካይሮን የውሃ የበላይነት ስጋትና ፍላጎት በግልጽ አንጸባርቀው ነበር። ይህ ንግግራቸው ግብፅ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት የመቆጣጠር ፍላጎቷንና ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ የልማት ፕሮጀክቶችን እንዳታካሂድ ለማድረግ የምታደርገው ሴራ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲያገኝ ዓላማ ያደረገ አደገኛ ንግግር ነው። በኋላም እ.ኤ.አ በ1993 ኤርትራን ከኢትዮጵያ በመገንጠል ሂደት ውስጥ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የስድስተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ ነበሩ። በወቅቱ 99 ነጥብ 8% የሚሆኑት ኤርትራዊያን በሕዝበ ውሳኔ ነጻ ሀገርንትን መርጠዋል በሚል ሕወሃትና ሻዕቢያ የሰሩት ድራማ ተቀባይነት አንዲያገኝ የተመድ ዋና ጸሐፊው ከፍተኛ ሴራ ሰርተዋል። ይህ የኤርትራ ህዝብን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በሻዕቢያ ባርነትና ግዞት እንዲማቅቅ ያደረገው የሕዝበ ውሳኔ ድራማ ላይ ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊ የመሪ ተዋናይነትን ሚና ተጫውተዋል። በሂደቱም ዋነኛ ዓላማቸው የሆነውን ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በሯን እንድታጣ አድርገዋል። ይህም የካይሮ የረጅም ጊዜ “ኢትዮጵያን የመዝጋት” ስትራቴጂ አካል እንደነበር ግልጽ ነው። የካይሮ መጥረቢያ እና አሁናዊው የጥፋት መንገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት የመጥረቢያ ተምሳሌታዊ ማብራሪያ፣ ሕገ ወጡ ሕወሃትን እንደ መጥረቢያ ብረት፤ ሻዕቢያን ደግሞ እንደ መጥረቢያ ዛቢያ ያስቀመጡ ሲሆን፤ መጥረቢያውን የሚያዘውና የሚወረውረው ሌላ ሶስተኛ አካል መኖሩንም ተናግረዋል። እንደሚታወቀው መጥረቢያ አንድን ነገር የመቁረጥና የማፍረስ ስራ ለማከናወን የሶስት አካላት ቅንጅት ያስፈልገዋል፦ ወርዋሪው (እጁ)፣ ዛቢያው (መያዣው) እና ብረቱ (ቁራጩ)። በዚህ ተምሳሌት ውስጥ ወርዋሪው ወይም መጥረቢያውን ጨብጦ ስራ ላይ የሚያውለው አካል ግብፅ ናት። ወርዋሪው ሁልጊዜም ከበስተጀርባ ሆኖ ስትራቴጂ ይነድፋል፣ ፋይናንስና ወታደራዊ ድጋፍ ያቀርባል፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሽፋን ይሰጣል። በሌላ በኩል የመጥረቢያ ብረት ያለ ዛቢያው (መያዣው) ኃይል አግኝቶ ማረፍ አይችልም፤ ዛቢያውም ያለ ወርዋሪው እጅ መንቀሳቀስ አይችልም። በዚህ ሂደት ሻዕቢያ (እንደ ዛቢያ) በቀጣናው ውስጥ የካይሮን ፍላጎት ለማስፈጸም የመያዣነት ሚና ይጫወታል። ቀጣናውን ለማተራመስ በሞመከር የካይሮን ስትራቴጂካዊ ፍላጎት ለማሳካት መንገድ ይከፍታል። ህገ-ወጡ ህወሓት ደግሞ እንደ መጥረቢያ ብረት በሀገር ውስጥ ሆኖ የሀገሪቱን መዋቅር፣ የህዝቦችን አንድነት እና ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ጥቅም ለመሸርሸር የሚሰራ ተላላኪ መሳሪያ ነው። በዚህ የሴራ ትስስር አሁን ላይ ኢትዮጵያ በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት ማደናቀፍ ዋነኛ ዓላማው አድርጎም እየሰራ ይገኛል። ግብፅ “የቀይ ባሕርና የኤደን ባሕረ-ሰላጤ የባሕር ወሰን ያላቸው ሀገራት ብቻ ናቸው በውሃው ላይ መወሰን ያለባቸው” የሚል መርህ በማንሳት፣ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትንና በቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኘውን ትልቁን ኢኮኖሚ (ኢትዮጵያን) ያገለለ ህገ-ወጥ ስብስብ ለመፍጠር እየሰራች ነው። በተጨማሪም በቅርቡ ከሶማሊያና ከሌሎች የአካባቢው ሀገራት ጋር የተደረጉ የውትድርናና የደህንነት ስምምነቶች፣ የሶማሊያን ሰላም ለማስጠበቅ ሳይሆን ቀጣናውን ለማተራመስና ወታደራዊ ስጋት ለመፍጠር የተቃኙ ናቸው። ይህ ሁሉ አካሄድ ዋነኛ ዓላማው ቀጣናውን የውክልና ጦርነት ማዕከል በማድረግና ኢትዮጵያ ወደ ባሕር እንዳትቀርብ ሆነ ተብሎ የተሰላ ሴራ ነው። ከቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ እስከ ዛሬው የቀይ ባሕር ሴራዎች ድረስ የተዘረጉት መረቦችም ይህንኑ እውነት ያሳያሉ። የካይሮ መጥረቢያዎችን ያዶለዶመው የመደመር መንግሥት ጥንካሬ ግብጽ እያከናወነችው ባለው አሁናዊ ሴራ ውስጥ የካይሮ ስትራቴጂስቶች የሳቱት ትልቅ እውነታ አለ። የግብጽ የሴራ መጥረቢያዎች ለመቁረጥ የሚሞክሩት በፈተናዎች የማትበገረውን እና እንደ ወርቅ በእሳት ውስጥ ተፈትና ያለፈችውን ኢትዮጵያን መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በታሪኳ የውጭ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎችን አሸንፎ መውጣት እንግዳ የሆነባት ሀገር አይደለችም። ባለፉት ክፍለ ዘመናት በወረራ፣ በውስጥ አለመረጋጋትና በጂኦፖለቲካዊ ከበባዎች ውስጥ አልፋ የጸናች ሀገር ናት። ወርቅ በእሳት ውስጥ ሲያልፍ ቆሻሻው ተወግዶ ይበልጥ እንደሚበራ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በተጋረጡባት የህልውና ፈተናዎች ሁሉ አልፋ ይበልጥ እየጠነከረችና እየተደራጀች መምጣቷ የታሪክ እውነታ ነው። አሁን ባለንበት ዘመን ደግሞ ይህ ጥንካሬዋ ይበልጥ ጎልብቷል። የመደመር መንግሥት ቁልፍ ፍልስፍና እና እየተገበራቸው ያሉ እርምጃዎች የካይሮን የረጅም ጊዜ የእጅ አዙር ጦርነትና ሴራዎችን ከንቱ ያደረገ ነው። የመደመር መንግሥት የውጭ ጫናዎችንና ሴራዎችን ለመመከት የመጀመሪያው ምሽግ የውስጥ አቅምን ማጠናከር መሆኑን በመገንዘብ፣ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለፍፃሜ ማብቃትና ግዙፍ የግብርና፣ የአረንጓዴ አሻራ እና የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን እውን አድርጓል። ይህም ግብፅ ኢትዮጵያን በልማት እንዳትበለፅግ ለማድረግ ያቀደችውን ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ አክሽፎታል። ካይሮ ኢትዮጵያን በጂኦፖለቲካዊ ከበባ ለማዳከምና በውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የነደፈችው የረጅም ጊዜ የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት ባስመዘገባቸው የልማትና የዲፕሎማሲ ድሎች ምክንያት ሙሉ በሙሉ ተደርምሷል። ይህ የጠላት ካምፕ መደርመስና የኪሳራ ስሌት ደግሞ በካይሮ ስትራቴጂስቶችና በውስጥ ተላላኪዎቻቸው (ባንዳዎች) ዘንድ ታላቅ ድንጋጤንና ተስፋ የመቁረጥ እሪታን ፈጥሯል። በመሆኑም የተበተነው የጠላት ካምፕና የተበሳጩት ባንዳዎች ብቸኛ አማራጭ አድርገው የያዙት በሳይበርና በሚዲያ ምህዳር የሃሰት መረጃዎችን ማንደድና የፕሮፓጋንዳ ማዕበል መፍጠር ቢሆንም፣ ይህም የተስፋ መቁረጥ ድምፅ ብክለት እንጂ የኢትዮጵያን የጽናት ጉዞ የሚያስተጓጉል አይሆንም። በሌላ በኩል ግብፅ “የቀይ ባሕር ሀገራት ጥምረት” በሚል ስም ቀጣናውን ለማተራመስና እርስ በርስ ጥርጣሬ ለመፍጠር የምታደርገውን የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት የጋራ እድገትና የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በማስቀደም በዲፕሎማሲው መስክ እየመከተው ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ምክክር የጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ በጋራ እንዲወስኑ በማድርግም የካይሮ ስትራቴጂስቶች በኢትዮጵያ የውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የጠነሰሱትን ሴራ ከንቱ አድርጎታል። በአጠቃላይ ታሪክ እንደሚነግረንና የወቅቱ እውነታ እንደሚመሰክረው፣ የግብፅ የሴራ መጥረቢያዎች በፈተናዎች እሳት ተፈትና ባላለፈች ደካማ ሀገር ላይ ያረፉ አይደሉም። ለመቁረጥ የሞከሩት በጽናት፣ በህዝቦቿ መስዋዕትነትና በፅኑ ታሪካዊ መሰረት ላይ የቆመችውን ኢትዮጵያን ነው። አሁን ላይ በመደመር መንግሥት መሪነት እየተገነባ ያለው የውስጥ አቅም፣ የልማት ስኬትና በራስ መተማመን የካይሮን የረጅም ጊዜ የከበባ ሴራ ሙሉ በሙሉ ወድቅ ማድረጉን ቀጥሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ሁሉ አሸንፎ ማለፍ የሰርክ ተግባሯ እንደመሆኑ መጠን፣ የዛሬውንም የጂኦፖለቲካ ውጥረትና የሴራ መረብ በጽናት አልፋ የቀጣናው የልማትና የሰላም ማዕከል ሆና መቀጠሏ የማይቀየር እውነት ነው።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 12364
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 21957
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14989
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20733
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 105185
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79828
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 58185
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55789
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 39871
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 39765
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 39239
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 37736
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 105185
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79828
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 58185
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55789
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ የማዕድን ምርት እመርታ
Aug 21, 2026 645
በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአገር በቀል የኢኮኖሚና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ታግዞ፣ ባለፉት ዓመታት የታዩበትን የአሰራርና መዋቅራዊ ችግሮች በመቅረፍ ከፍተኛ የመነቃቃት ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ዘርፉ በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ ማዕድን በብዝኃ ዘርፍ የልማት ምልከታችን ውስጥ እና በሀገሪቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል። ባለፉት ሶስት አሥርት ዓመታት ውስጥ የማዕድን ዘርፉ ለአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያበረከተው አስተዋጽኦ ከ0 ነጥብ 8 በመቶ በታች የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ግን መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው የላቀ ትኩረት ከፍተኛ መዋቅራዊ ሽግግር እያመጣ ይገኛል። በ2018 በጀት ዓመት ከዘርፉ 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ተችሏል። ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ92 በመቶ የገቢ ዕድገትና የ27 በመቶ የምርት መጠን ብልጫ ያሳየ ሲሆን፣ ምርቶቹም በዋናነት ወደ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ አሜሪካ፣ ጀርመን እና ቻይና ተልከዋል። በወጪ ንግድ እድገት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው የወርቅ ምርት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ለውጭ ገበያ የቀረበ ሲሆን እስከ ዓመቱ ማብቂያ 32 ቶን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።   በባህላዊ መንገድ የሚመረተውን የወርቅ ምርት ለማዘመንም መንግሥት የማጣሪያና ማቀለጫ ፋብሪካዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል። የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ከውጭ የሚገቡ ስትራቴጂክ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህም ለድንጋይ ከሰል ግዢ ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት የተቻለ ሲሆን፣ የሲሚንቶ ምርትም ባለፉት ስምንት ዓመታት ከነበረበት 8 ሚሊየን ቶን አሁን ላይ በዓመት ወደ 14 ሚሊየን ቶን አድጓል። ሀገሪቱ በየዓመቱ ለማዳበሪያ ግዢ የምታወጣውን 2 ቢሊየን ዶላር ለማስቀረትም የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ተጀምሯል። በተጨማሪም በየዓመቱ ለብረት ምርት ግዢ የሚወጣውን 1 ቢሊየን ዶላር በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት የሚያስችል ግዙፍ ፋብሪካ የመገንባት ስምምነት ተፈጽሞ ወደ ስራ ተገብቷል። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በዘርፉ የተሰማሩ ፕሮጀክቶች ዋጋ 10 ቢሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከለውጡ በፊት ከነበረውና ከ100 ሚሊየን ዶላር የማይበልጡ አነስተኛ ኢንቨስትመንቶች በከፍተኛ ደረጃ የለወጠ ስኬት ነው። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በአፋር ክልል የሚገኘውን ግዙፍ የፖታሽ ክምችት ለማልማት ፈቃድ አግኝቶ ወደ ሥራ ገብቷል። በተጨማሪም ታንታለምን እሴት ጨምሮ ለመላክ ከአሜሪካ ኩባንያ ጋር ድርድር እየተደረገ ሲሆን፣ ለባትሪና ቴክኖሎጂ ወሳኝ የሆኑትን ሊቲየም፣ ኮባልትና ኒኬልን ለማምረት ዝግጅት ተጠናቋል። የኢንቨስትመንት ምህዳሩን ሳቢ ለማድረግ የማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ አሰራር ቅድሚያ የመጣን ቅድሚያ ማስተናገድ በሚል መርህ እንዲመራ ተደርጓል። የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና መላኪያ ፈቃዶች፣ እንዲሁም የካዳስተር ሲስተም ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ አሰራር ተሸጋግረዋል። በ2019 በጀት ዓመት ከዘርፉ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፣ የመንግሥት ስትራቴጂካዊ እቅድ እ.አ.አ. በ2030 የማዕድን ወጪ ንግድ ገቢን ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ በማድረስ ኢትዮጵያን ከአፍሪካ አምስት ቀዳሚ የማዕድን አምራች ሀገራት ተርታ ማሰለፍ ነው።   በዘርፉ እየተካሄደ ያለው መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ በውጭ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኝነት በመቀነስ ወደ ኢንዱስትሪ መሪነት የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥነዋል። የወርቅ፣ የተፈጥሮ ጋዝ፣ የፖታሽ እና የቴክኖሎጂ ማዕድናት በሀገር ውስጥ እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ላይ የሚኖራትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ያረጋግጣል።
የአረቡ ዓለም ከግብፅ ምን አተረፈ?
Aug 19, 2026 609
የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ አካሄድ በታሪካዊ እውነታዎች እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ላይ እየተመሠረተ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ ጊዜ ያለፈባቸው የጂኦ ፖለቲካዊ የመጠላለፍ አካሄዶች ዋጋ ቢስነትና ጥቅም አልባነት በግልጽ እየታየ ይገኛል። ለብዙ አስርት ዓመታት ግብፅ የዓረብ ሊግን ለራሷ ጠባብ ፍላጎቶች እና ጂኦፖለቲካዊ አጀንዳዎች ማስፈጸሚያነት በሰፊው ስትጠቀምበት ቆይታለች። ሆኖም ይህ ጥቅምና ጉዳትን ብቻ መሰረት ያደረገ ግንኙነት አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ያስነሳል፦ ለመሆኑ የዓረቡ ዓለም ከግብፅ በምላሹ ያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? ለዚህ ጥያቄ አጭሩ መልስ ምንም የሚል ነው ሲል “What Has the Arab World Gained from Egypt? Why Ethiopia Belongs in the Arab League?” ፀሐፊው እና በፖለቲካና ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ በቋሚነት የሚተነትነው አስተያየት የሚሰጠው ጅብሪል ላሞ በኢዜአ እንግሊዘኛ ገጽ ባሳፈረው ሐተታ ላይ ፣ የግብጽ ፖሊሲዎች እንዲሁም ለሁለት አስርት ዓመታት የዘለቀው አምባገነናዊ አስተዳደር የጋራ ጥንካሬን ከመፍጠር ይልቅ የቀጣናውን አለመረጋጋት ማባባሳቸውን ገልጿል። እነዚህ ፖሊሲዎች፣ በምሥራቅ አፍሪካ እና በቀይ ባሕር አካባቢም ውጥረትን እያባባሱ እንደሚገኙ አመልክቷል። እነዚህ አካባቢዎች ለዓረቡ ዓለም የራቁ አይደሉም፤ ይልቁንም ለዓረቡ ዓለም ደኅንነት፣ የባሕር ንግድ፣ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የምግብ ዋስትና እጅግ ወሳኝ እና ስትራቴጂካዊ ማዕከላት ናቸው። የግብፅ ከፋፋይ ቀጣናዊ አካሄድ ከታዩባቸው ጉልህ ማሳያዎች አንዱ በኤርትራ ጉዳይ እና በሰፊው የኢትዮጵያ ግዛት አንድነት ላይ የነበራት ታሪካዊ ጣልቃ ገብነት ነው። ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ቀጣናዊ ተፅዕኖዋን ለመግታት በግብጽ ታስበው የተደራጁ ተገንጣይ ኃይሎችን እና ፖለቲካዊ ፕሮጀክቶችን በግልጽ ትደግፍ እንደነበረ ፀሐፊው አውስቷል። ከኢትዮጵያ የኤርትራ መገንጠል በምሥራቅ አፍሪካ ቀውስ የተሞላ ታሪክ ውስጥ አቢይ ክስተት ሲሆን፣ የውጭ ጂኦፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነቶች የሀገራትን እጣ ፈንታ እንዴት እንደሚያናጉ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የዲፕሎማሲ ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ የቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ እና የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ፣ ኢትዮጵያን ለማዳከም ታስቦ የተዘረጋውን የኤርትራን የመገንጠል ፕሮጀክት በመደገፍና በማፋጠን ረገድ ትልቅ ሚና ነበራቸው። በተጨማሪም ግብጽ በደቡባዊ የቀይ ባህር ቀጣና የምታካሂደው ቀውስ የመፍጠር እንቅስቃሴ፣ ለዓለም አቀፍ የባህር ንግድና ለቀጣናው ደህንነት ቀጥተኛ ስጋት ደቅኗል። በባብ-ኤል-ማንደብ የባሕር ወሽመጥ አካባቢ ውጥረቶችን በመቀስቀስ እና ተላላኪ ታጣቂ ቡድኖችን በማንቀሳቀስ፣ ወሳኝ የሆኑ የባህር መተላለፊያዎችን የጂኦፖለቲካዊ ግጭት መድረክ አድርጋዋለች። ይህም ለጠቅላላው የዓረብ ዓለም የኢነርጂና የምግብ አቅርቦት መሰረት የሆነውን የደህንነት መዋቅር አደጋ ላይ ጥሎታል፤ ሲሉ ጅብሪል ላሞ ያብራራሉ። ጅብሪል ላሞ በጽሑፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ የግብፅ ግልጽ የራስ ወዳድነት እንቅስቃሴዎች ቀጣናዊ ውጥረትን የሚፈጥሩ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ መቀላቀል ግን ለዓረቡ ዓለም እጅግ ከፍተኛ ጥቅም የሚያስገኝ ለውጥ አምጪ ዕድል ይዞ ይመጣል። በመደመር ፍልስፍና አሳታፊ ማዕቀፍ ሥር፣ ኢትዮጵያ ከማግለል ፖሊሲ ይልቅ የዓረቡን ዓለም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማስተሳሰር የሚያስችል የላቀ የዲፕሎማሲ አቅም አላት። በዚህም የአፍሪካ ዋነኛ የዲፕሎማሲ ማዕከል እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ የባለብዙ ወገን ትብብሮችን በመቅረጽ ረገድ ያላትን የካበተ ልምድ ታካፍላለች። የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ የመቀላቀል ጥረት ጊዜያዊ የፖለቲካ ስሌት ሳይሆን፣ የተፈጥሮ የታሪክ ጥሪ ነው። ከ135 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ፣ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እና ጥልቅ የሥልጣኔ መሠረት ያላት ይህች የቀይ ባሕር ሀገር፣ አባልነቷ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ መካከል ስትራቴጂካዊ ድልድይ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር ያላት ቁርኝት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በጋራ ታሪክ፣ ባህል እና የደም ትስስር ላይ የተገነባ ነው። እንደ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሉ የትምህርት ተቋማት፣ የኢትዮጵያ ጥናቶች በታሪክ ደረጃ ከመካከለኛው እና ከቅርብ ምሥራቅ ታሪክ (Near Eastern Studies) ተመድቦ መጠናቱ፤ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ከቀጣናው ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ ውህደት የሚያረጋግጥ ሕያው ማሳያ ነው። የባብ-ኤል-ማንደብ የባህር ወሽመጥ በጭራሽ መሰናክል አልነበረም፤ ይልቁንም ንግድን፣ ባህልን እና ማህበረሰቦችን በቀይ ባሕር በኩል ያገናኘ ዋንኛ መተላለፊያ ሆኖ አገልግሏል። ከንጉሥ አብረሃ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ በኢትዮጵያውያን እና በመካከለኛው ምሥራቅ ሕዝቦች መካከል የጋራ የደም ትስስር እንደነበር የሚያረጋግጡ ዘመናዊ የስነ ህይወት( ጄኔቲክስ) ጥናቶች፣ የዚህን ታሪካዊ ቁርኝት እውነተኛነት በግልጽ ያሳያሉ። በቋንቋና በባህል ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት መሠረት ታሪካዊ ትስስር ያለው ነው። የሀገሪቱ የቋንቋና የሥነ-ጽሑፍ ውርስ ከዓረብኛ፣ አራማይክና ዕብራይስጥ ጋር በጽኑ የተሳሰረ ሲሆን፣ ይህም በምሥራቅ አፍሪካና በአረቢያ ልሳነ-ምድር መካከል ያለውን ጥልቅ የጋራ የሥልጣኔ ቁርኝት ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ አላት። የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ተስደው በንጉስ ነጃሺ ከለላ ማግኘታቸው የእስልምናን ህልውና የታደገ ታሪካዊ ክስተት ሲሆን፣ ይህም ሀገሪቱን ከዓረቡ ዓለም ጋር በጽኑ አስተሳስሯታል። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ የዓረብ ሊግን በኢትዮጵያ ላይ እንደ ተቋማዊ ተፅዕኖ ማሳደሪያ መሣሪያ ግብጽ ስትጠቀምበት ቆይታለች። ግብፅ የውጭ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ዕድገት፣ የህዳሴውን ግድብም ሆነ የባሕር በር ጥያቄን እንደ ሥጋት በሚያይ ጊዜ ያለፈበት ስሌት ላይ የተመሠረተ ነው። ግብፅ የራሷን የውሃ አቋም በሊጉ ላይ በመጫን፣ ተቋሙ ከኢትዮጵያ ጋር አላስፈላጊ ውጥረት ውስጥ እንዲገባ አድርጋለች። ጅብሪል ላሞ እንዳመለከተው፣ ከግብጽ የአግላይነት ፖሊሲ ይልቅ የዘመኑ ነባራዊ ሁኔታዎች ሙሉ ትብብርን የሚጠይቁ ናቸው። በመደመር መርህ፣ ኢትዮጵያ ለዓረቡ ዓለም ለዘመናት ከቆዩ የጥላቻ መንገዶች በላቀ ሁኔታ የተሻሉ ጥቅሞችን ማቅረብ ትችላለች። እያደገ የመጣው የኢንዱስትሪ እና የአረንጓዴ ኃይል አቅሟ፣ ኢትዮጵያን ለቀይ ባህር ቀጣና የመረጋጋት ምሰሶ አድርጓታል። የመካከለኛው ምሥራቅ ቀጣና የውሃ እጥረት እና የምግብ ዋስትና ሥጋት በተጋረጠበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ የውሃ ሀበት እና ለም መሬት ለቀጣናው ወሳኝ የግብርና-ኢንዱስትሪ አጋር ያደርጋታል። የዓረብ ሊግ አባል ሀገራት የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ብሔረተኝነት በመሻገር፣ የቀይ ባህርን ቀጣና የሥልጣኔ እውነታ መቀበል ይኖርባቸዋል። አረብ ሊግ እንደ ጅቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ኮሞሮስ እና ሞሪታኒያ አባል ሀገራት መያዙ፣ ስብስቡ የተለያዩ ቀጣናዊ እውነታዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑን ያሳያሉ። የዓረብ ሊግ ሙሉ አባልነት የኢትዮጵያን አፍሪካዊ ማንነት ሳይቀንሰው፣ አህጉሩን ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር የሚያገናኝ ዋነኛ ድልድይ የሚያደርጋት በመሆኑ፤ ሊጉ የኢትዮጵያን አጋርነት በመቀበል ለአዲስ አበባ ተገቢውንና ሕጋዊ ቦታዋን የሚሰጥበት ጊዜ አሁን እንደሆነ በመግለጽ ጅብሪል ላሞ ፅሁፉን ቋጭቷል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም