ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት ነው
Sep 16, 2026 190
አዲስ አበባ፤ መስከረም 6/2019 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ መጀመርን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት በመላው ሀገሪቱ ለሚገኙ ተማሪዎች አዲሱ የትምህርት ዘመን ስኬታማ እንዲሆን ተመኝተዋል። ‎‎ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን እያንዳንዱ ተማሪ ለላቀ እውቀት በትጋትና ጉጉት ትምህርቱን መከታተልና ለጥሩ ውጤት በጽናት መትጋት እንደሚጠበቅበት ገልጸዋል። አዲሱ ትዉልድ የሀገሪቱን የወደፊት ዕድል መቅረጽ በሚያስችሉ ክህሎቶች እንዲገነባም አበረታተዋል። ‎‎በሃገሪቱ ዛሬ እየተተገበሩ የሚገኙት በርካታ የልማት ሥራዎች የነገን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ በመሆናቸው ትዉልዱ የዚህ ቀጣይ ዕድል ተጠቃሚ እና ባለአደራ መሆን ይኖርበታል ብለዋል።   የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ‎‎ብቁ እና በራሱ የሚተማመን ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመምህራኖች ትጋትና መሰጠት መሰረታዊ ምሰሶ መሆኑንም አንስተዋል። ተማሪዎችን ማነቃቃት፣ አቅማቸውን ማውጣት፣ እንዲሁም ነገ ተፎካካሪ ሆነው እንዲወጡ የሚያስችሏቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና እሴቶችን የማስታጠቅ አደራን እንዲያስቀጥሉም በትህትና አሳስበዋል። ‎‎በትምህርት ዘርፉ ውስጥ የሚገኙ ባለድርሻ አካላትም ስኬታማ እና ፍሬያማ የትምህርት ዘመን እንዲሆን የበኩላቸዉን ሃላፊነት እንዲወጡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል።
አርሰናል እና ሊቨርፑል በካራባኦ ካፕ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ
Sep 16, 2026 154
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ የሶስተኛ ዙር ጨዋታዎች ማምሻውን ተካሄደዋል። በፖርትማን ሮድ በተደረገው ጨዋታ አርሰናል ኤፕስዊች ታውንን 4 ለ 2 ረትቷል። የ16 ዓመቱ ታዳጊ ማክስ ዶውማን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኖኒ ማዱዌኬ እና ሚኬል ሜሪኖ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። አኒስ ሜህመቲ እና ቹባ አክፖም የኤፕስዊችን ግቦች አስቆጥረዋል። በሌላኛው መርሐ ግብር ሊቨርፑል ቶተንሃም ሆትስፐርስን 3 ለ 1 አሸንፏል። በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አሌክሲስ ማካሊስተር፣ ኮዲ ጋፕኮ እና ዶምኒክ ስቦዝላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ኮኖር ጋላገር የቶተንሃምን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ብሬንትፎርድ ሬዲንግን 2 ለ 1፤ ፉልሃም ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 2 አሸንፈዋል። ፒተርቦሮው ባርንስሌይን በመለያ ምት ረትቷል። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል፣ ሊቨርፑል፣ ብሬንትፎርድ፣ ፉልሃም እና ፒተርቦሮው ወደ አራተኛ ዙር አልፈዋል።
የግብርና ምርት እሴት ሰንሰለትን ለማሻሻል ትብብርና የፖሊሲ ማዕቀፍ መተግበር ይገባል - ኢጋድ
Sep 15, 2026 317
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፡- በአባል ሀገራት ቀጣና የግብርና ምርትን ለማሻሻልና እሴት ለመጨመር ትብብርን በማጠናከርና ሊያግባባ የሚችል የጋራ የፖሊሲ ማዕቀፍ መተግበር እንደሚገባ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ገለጸ። ኢጋድ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ከ2026 እስከ 2035 ለ10 ዓመታት የሚተገብረውን የቀጣናው የግብርና ምርት የምግብ ሥርዓት ኢንቨስትመንት ዕቅድ የባለሙያዎች ግምገማና በሚኒስትሮች የማጽደቅ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው። የኢጋድ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አቅም ፕሮግራም አስተባባሪ ሰናይት ረጋሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢጋድ ቀጣና ሀገራት እንደ ጎርፍ፣ ድርቅና መሰል የተፈጥሮ አደጋዎችን በተደጋጋሚ የሚያስተናግዱ ናቸው። የአፍሪካ መሪዎች እ.ኤ.አ. በ2025 በዩጋንዳ ካምፓላ ተገናኝተው የምግብ ሥርዓት ግንባታ አቅም ስምምነት ሰነድ በመፈራረም ለትግበራው ቁርጠኝነታቸውን ማሳየታቸውን አስታውሰዋል።   በዚህም በአህጉር፣ በቀጣናና በሀገር ደረጃ ገቢራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ መደረጉን ገልጸው፤ የኢጋድ የግብርና ምርት የምግብ ሥርዓት ኢንቨስትመንት የ10 ዓመት ዕቅድ የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል። ከምግብ ዋስትና ጋር የተያያዙ ችግሮች በሀገር ደረጃ ብቻ የሚፈቱ አለመሆናቸውን ገልጸው፤ የ10 ዓመት ዕቅዱ የሀገራትን የጋራ ትብብር እንደሚያጠናክር ብለዋል። ለአብነት የበረሃ አንበጣ በቀጣናው ቢከሰት አንድ ሀገር ብቻውን የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አይችልም ያሉት አስተባባሪዋ፤ የቀጣናው ሀገራት በጋራ ጉዳዮች ላይ የጋራ መፍትሔና እርምጃ መውሰድ የሚችሉበትን ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ዕቅዱ ሀገራት በተናጠል ከራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት ከሚወስዷቸው የመፍትሔ አማራጮች ባለፈ ትብብራቸውን ማጠናከርና የዕውቀት ሽግግር መፍጠር እንደሚያስችልም ተናግረዋል። የኢጋድ የግብርና ምርት የምግብ ሥርዓት ኢንቨስትመንት ዕቅድ የግብርና ምርትን ከማሳደግ ባለፈ እሴት መጨመር የሚቻልበትን አቅም መገንባት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።   ድርቅ በሚከሰትበት ወቅት ቅድመ ማስጠንቀቂያ መስጠት፣ የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ፣ ድንበር ተሻጋሪ በሽታዎችን በጋራ መከላከል የሚችሉበት ሥርዓት እንዲዘረጋ ድጋፍ ማድረግ ያስችላል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ የቀጣናው ሀገራት የሚስማሙበትን እና ግብራዊ ሊያደርጉት የሚችለውን የጋራ ቀጣናዊ የፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። የግብርና ሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪና የአፍሪካ ልማት ፕሮግራም ተወካይ ዜና ሀብተወልድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከአፍሪካና ከቀጣናው ሀገራት ጋር የተናበበ ዕቅድ በመተግበር በአርዓያነት የሚጠቀስ ውጤት አስመዝግባለች ብለዋል። በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴ ልማት እንዲሁም አሁን በስፋት ግብራዊ በተደረገው የሩዝ ልማት ተጨባጭ ለውጥ መገኘቱን ገልጸዋል። ግብርና የአፍሪካ የልማት ሞተር መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ይሄንን ታሳቢ ያደረገ የግብርና ዕመርታ አምጥታለች ብለዋል። በቀጣይም ኢትዮጵያ በካምፓላ ስምምነትና በኢጋድ የ10 ዓመት የኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ በመመስረት የቀጣይ 10 ዓመት የተናበበ ዕቅድ በማውጣት ግብራዊ እንደምታደርግ ገልጸዋል። ኢጋድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለቀጣናው ሀገራት የምግብ ዋስትና መረጋገጥና በሽታ መከላከል ሥርዓት ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ ቀጣናዊ ትብብርና ተቋማዊ አንድነትን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
በሐረሪ ክልል በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Sep 15, 2026 320
ሐረር፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የክልሉ አመራሮች በክረምቱ ወራት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ አከናውነዋል። በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሮች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚሰጡ ችግኞች መተከላቸው ይታወሳል። በችግኝ ተከላው የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የመከላከያና ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ አርሶ አደሮች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ መሆናቸውም እንዲሁ። በዛሬው እለትም ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች 'በሃኪም' ጋራ በመገኘት የተከሏቸውን ችግኞች ውሃ የማጠጣት እና የመንከባከብ ሥራ አከናውነዋል። በክልሉ በክረምቱ ወራት የተተከሉት ችግኞች ወደ ዛፍነት እስኪቀየሩ ድረስ አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው ይገኛል። ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንዳሉት፣ በክልሉ በክረምቱ ወቅት የተተከሉት ችግኞች በአግባቡ እንዲጸድቁ አስፈላጊውን እንክብካቤ ማድረግ አስፈላጊ ነው። በአሁኑ ወቅትም በተለይ የተተከሉ ችግኞች ለሚፈለገው ዓላማ እንዲበቁ እየሰሩ የሚገኙ አካላትን አበረታተዋል። በቀጣይም ችግኞቹን ውሃ በማጠጣትና በመኮትኮት እንዲፀድቁ ማድረግ እንደሚገባም ነው ርዕሰ መስተዳድሩ ያሳሰቡት። ከዚህ በተጨማሪ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የሃኪም ጋራ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክት የስራ እንቅስቃሴን ተዘዋዉረው ተመልክተዋል።   የፕሮጀክቱ ስራ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑንም አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ማንሰራራት የአፍሪካን ሕዳሴ ያበስራል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Sep 15, 2026 410
ኢትዮጵያ አዲሱን ዓመት ብሔራዊ ጥቅሞቿን በማስቀደምና የአፍሪካውያን እውነተኛ ድምፅ በመሆን ጀምራዋለች። በዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ የጂኦፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ጽኑና ገለልተኛ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን በመከተል የብሪክስ አባል መሆን የቻለችው ኢትዮጵያ፣ በሕንድ ኒው ዴልሂ በተካሄደው 18ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ ላይ አህጉራዊ አርአያነቷንና ስትራቴጂካዊ ተሰሚነቷን በተግባር አስመስክራለች። “ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት” በሚል መሪ ቃል የተካሄደው ይህ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ ከአባልና አጋር ሀገራት ጋር ያላትን ሁለገብ ትስስር ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገረና ፍትሃዊና አካታች ዓለም አቀፍ ሥርዓት እንዲገነባ ያላትን ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ምዕራፍ ሆኗል።   ኢትዮጵያ በጉባኤው መድረክ ላይ ባነጸባረቀችው አቋም፣ ሀገራት ቀውሶች ከመከሰታቸው በፊት የመቋቋም አቅም ሊገነቡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥታለች። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ባደረገችው ጥረት ከውጭ ለእርዳታ ከሚገባ የስንዴ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ መላቀቋን ይፋ ያደረገች ሲሆን የብሪክስ የሰብል ልውውጥ ማዕቀፍ (BRICS Grain Exchange) እንደ አምራችም ሆነ አቅራቢ ሆና ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። በመድረኩ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂና ፈጠራ ዘርፍ የዲጂታል መሠረተ ልማት፣ ዲጂታል መታወቂያ፣ የክፍያ ሥርዓቶች እና አስተማማኝ የመረጃ ልውውጥ አውታሮችን በስፋት እየገነባች መሆኗን አስገንዝባለች። ለአፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት ለመምራት የሚያስችለውን «የመደመር ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ» እያቋቋመች መሆኗን በመግለጽ፣ ከብሪክስ ተቋማት ጋር በጋራ ለመሥራት ያላትን ዝግጁነት አረጋግጣለች።   አፍሪካ የበርካታ ማዕድናት ሀብት ባለቤት መሆኗን በማስታወስም፣ የማዕድን ሀብት ለኢነርጂ ሽግግር፣ ለላቀ ማኑፋክቸሪንግ እና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ወሳኝ መሆኑን ኢትዮጵያ አንጸባርቃለች። የብሪክስ አባል ሀገራት የካፒታል፣ የቴክኖሎጂ እና የገበያ አማራጭ በመያዛቸው እነዚህን ሀብቶች አቀናጅቶ ለመጠቀምና በጥሬ ሀብቱ ላይ እሴት ለመጨመር ትልቅ እድል እንደሚፈጥር አመልክታለች። ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የማምረት አቅሟን እያስፋፋች መሆኗን፣ እንዲሁም በማዕድናት፣ በታዳሽ ኢነርጂ እና እያደገ ባለው የኢንዱስትሪ አቅም ላይ አጋርነቶችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ትልቅ ዕድል መሆኑን፣ ለጎረቤት ሀገራት የሚደረገው የኃይል አቅርቦት እና አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ መሆኗ ለአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ትስስር ያላትን አበርክቶ በግልጽ በማስመዝገብ መድረኩን ተጠቃማበታለች። ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እያከናወነችና የውጭ ዕዳዋን ለማሸጋሸግ እየሰራች መሆኗን ገልጻ፤ በፈተና ውስጥ ለሚገኙ ኢኮኖሚዎች የዕዳ አከፋፈል ሂደት ፈጣን፣ ግልጽ እና ተገማች መሆን እንዳለበት አሳስባለች። እንዲሁም በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ያላቸው ውክልና ፍትሃዊ፣ ተደማጭነታቸውን ያረጋገጠ እና ተጨባጭ ውጤት የሚያመጣ መሆን እንዳለበት ጠንካራ ጥሪ አቅርባለች። በጉባኤው ባደረገችው ንቁ ተሳትፎም ሀገራችን የዓለም ንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን፣ በዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ምክር ቤት ተጨማሪ መቀመጫ እንድታገኝ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) በአዲስ አበባ እንድታዘጋጅ ድጋፍ አግኝታለች፤ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (NDB) ቢሮ በአዲስ አበባ እንዲከፈት እና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ወደ ስምምነት የሚቀይር «የብሪክስ አስተባባሪ» እንዲቋቋም ያቀረበቻቸው ምክረ ሀሳቦች ሰፊ ተቀባይነት አግኝተዋል። ከብሪክስ መድረክ ጎን ለጎን ከተከናወኑ ሰፊ የዲፕሎማሲ ሥራዎች መካከል ከዓለም መሪዎች ጋር የተደረጉት ውይይቶች ሀገራዊ ጥቅሞችን ከማስጠበቅና አጋርነትን ከማጠናከር አንፃር ትልቅ ስኬት የተመዘገበባቸው ነበሩ። ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በኢትዮጵያና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት ተደርጓል። ውይይቱ በመከላከያና ደኅንነት፣ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እንዲሁም በባህልና ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት መስኮች ያለውን ትብብር ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነት የተረጋገጠበት ነበር። በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረገው ዝግጅት፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብራችንን ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት መፍጠር ተችሏል። ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋርም በመከላከያ ትብብር ማሳደግ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በአቅም ግንባታ እና በማዕድን ልማት ዙሪያ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤ የዘመናት ታሪካዊ ትስስራችንን ወደተግባራዊ የኢኮኖሚና ልማት ምዕራፍ ማሸጋገር ተችሏል። በተጨማሪም ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ጋር በኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝም፣ የታዳሽ ኃይል አጋርነትና በአምራች ዘርፍ ተሞክሮዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጎ ለሀገር ውስጥ ልማት የሚሆን ትልቅ በር ተከፍቷል። ከአቡ ዳቢ አልጋ ወራሽ ልዑል ሼህ ኻሊድ ቢን ሙሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር በብሪክስ ቅድመ-አጀንዳዎችና በሁለገብ ትብብር ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ጋርም በቀይ ባሕር አካባቢ ወቅታዊ ሁነቶች እና በቀጣናው የደኅንነት መረጋጋት እንዲሁም በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ የንግድ፣ የኢኮኖሚና ልማት ልውውጦቻችንን ይበልጥ ለማስፋፋት በጋራ ለመሥራት ስምምነት ላይ ተደርሷል። በአጠቃላይ፣ ኢትዮጵያ በ18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ያከናወነቻቸው ስትራቴጂካዊ የዲፕሎማሲ ሥራዎችና ያስመዘገበቻቸው ተጨባጭ ውጤቶች የሀገሪቱን የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን እውን የሚያደርጉ ወሳኝ ምሶሶዎች ናቸው። መንግሥት በዚህ ታሪካዊ መድረክ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነቷን በመጠቀም ስትራቴጂካዊ ጥቅሟን በድፍረት የምትጠይቅ፤ ለአፍሪካ ልማት፣ ሰላም እና ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ ትብብር የቆመች አስተማማኝ አጋር መሆኗን በተግባር አስመስክሯል። የኢትዮጵያ ማንሰራራት የአፍሪካን ሕዳሴ ያበስራል!
የሚታይ
የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት ነው
Sep 16, 2026 190
አዲስ አበባ፤ መስከረም 6/2019 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ መጀመርን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት በመላው ሀገሪቱ ለሚገኙ ተማሪዎች አዲሱ የትምህርት ዘመን ስኬታማ እንዲሆን ተመኝተዋል። ‎‎ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን እያንዳንዱ ተማሪ ለላቀ እውቀት በትጋትና ጉጉት ትምህርቱን መከታተልና ለጥሩ ውጤት በጽናት መትጋት እንደሚጠበቅበት ገልጸዋል። አዲሱ ትዉልድ የሀገሪቱን የወደፊት ዕድል መቅረጽ በሚያስችሉ ክህሎቶች እንዲገነባም አበረታተዋል። ‎‎በሃገሪቱ ዛሬ እየተተገበሩ የሚገኙት በርካታ የልማት ሥራዎች የነገን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ በመሆናቸው ትዉልዱ የዚህ ቀጣይ ዕድል ተጠቃሚ እና ባለአደራ መሆን ይኖርበታል ብለዋል።   የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ‎‎ብቁ እና በራሱ የሚተማመን ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመምህራኖች ትጋትና መሰጠት መሰረታዊ ምሰሶ መሆኑንም አንስተዋል። ተማሪዎችን ማነቃቃት፣ አቅማቸውን ማውጣት፣ እንዲሁም ነገ ተፎካካሪ ሆነው እንዲወጡ የሚያስችሏቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና እሴቶችን የማስታጠቅ አደራን እንዲያስቀጥሉም በትህትና አሳስበዋል። ‎‎በትምህርት ዘርፉ ውስጥ የሚገኙ ባለድርሻ አካላትም ስኬታማ እና ፍሬያማ የትምህርት ዘመን እንዲሆን የበኩላቸዉን ሃላፊነት እንዲወጡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሐረሪ ክልል በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Sep 15, 2026 320
ሐረር፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የክልሉ አመራሮች በክረምቱ ወራት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ አከናውነዋል። በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሮች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚሰጡ ችግኞች መተከላቸው ይታወሳል። በችግኝ ተከላው የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የመከላከያና ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ አርሶ አደሮች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ መሆናቸውም እንዲሁ። በዛሬው እለትም ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች 'በሃኪም' ጋራ በመገኘት የተከሏቸውን ችግኞች ውሃ የማጠጣት እና የመንከባከብ ሥራ አከናውነዋል። በክልሉ በክረምቱ ወራት የተተከሉት ችግኞች ወደ ዛፍነት እስኪቀየሩ ድረስ አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው ይገኛል። ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንዳሉት፣ በክልሉ በክረምቱ ወቅት የተተከሉት ችግኞች በአግባቡ እንዲጸድቁ አስፈላጊውን እንክብካቤ ማድረግ አስፈላጊ ነው። በአሁኑ ወቅትም በተለይ የተተከሉ ችግኞች ለሚፈለገው ዓላማ እንዲበቁ እየሰሩ የሚገኙ አካላትን አበረታተዋል። በቀጣይም ችግኞቹን ውሃ በማጠጣትና በመኮትኮት እንዲፀድቁ ማድረግ እንደሚገባም ነው ርዕሰ መስተዳድሩ ያሳሰቡት። ከዚህ በተጨማሪ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የሃኪም ጋራ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክት የስራ እንቅስቃሴን ተዘዋዉረው ተመልክተዋል።   የፕሮጀክቱ ስራ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑንም አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ማንሰራራት የአፍሪካን ሕዳሴ ያበስራል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Sep 15, 2026 410
ኢትዮጵያ አዲሱን ዓመት ብሔራዊ ጥቅሞቿን በማስቀደምና የአፍሪካውያን እውነተኛ ድምፅ በመሆን ጀምራዋለች። በዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ የጂኦፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ጽኑና ገለልተኛ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን በመከተል የብሪክስ አባል መሆን የቻለችው ኢትዮጵያ፣ በሕንድ ኒው ዴልሂ በተካሄደው 18ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ ላይ አህጉራዊ አርአያነቷንና ስትራቴጂካዊ ተሰሚነቷን በተግባር አስመስክራለች። “ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት” በሚል መሪ ቃል የተካሄደው ይህ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ ከአባልና አጋር ሀገራት ጋር ያላትን ሁለገብ ትስስር ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገረና ፍትሃዊና አካታች ዓለም አቀፍ ሥርዓት እንዲገነባ ያላትን ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ምዕራፍ ሆኗል።   ኢትዮጵያ በጉባኤው መድረክ ላይ ባነጸባረቀችው አቋም፣ ሀገራት ቀውሶች ከመከሰታቸው በፊት የመቋቋም አቅም ሊገነቡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥታለች። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ባደረገችው ጥረት ከውጭ ለእርዳታ ከሚገባ የስንዴ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ መላቀቋን ይፋ ያደረገች ሲሆን የብሪክስ የሰብል ልውውጥ ማዕቀፍ (BRICS Grain Exchange) እንደ አምራችም ሆነ አቅራቢ ሆና ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። በመድረኩ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂና ፈጠራ ዘርፍ የዲጂታል መሠረተ ልማት፣ ዲጂታል መታወቂያ፣ የክፍያ ሥርዓቶች እና አስተማማኝ የመረጃ ልውውጥ አውታሮችን በስፋት እየገነባች መሆኗን አስገንዝባለች። ለአፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት ለመምራት የሚያስችለውን «የመደመር ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ» እያቋቋመች መሆኗን በመግለጽ፣ ከብሪክስ ተቋማት ጋር በጋራ ለመሥራት ያላትን ዝግጁነት አረጋግጣለች።   አፍሪካ የበርካታ ማዕድናት ሀብት ባለቤት መሆኗን በማስታወስም፣ የማዕድን ሀብት ለኢነርጂ ሽግግር፣ ለላቀ ማኑፋክቸሪንግ እና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ወሳኝ መሆኑን ኢትዮጵያ አንጸባርቃለች። የብሪክስ አባል ሀገራት የካፒታል፣ የቴክኖሎጂ እና የገበያ አማራጭ በመያዛቸው እነዚህን ሀብቶች አቀናጅቶ ለመጠቀምና በጥሬ ሀብቱ ላይ እሴት ለመጨመር ትልቅ እድል እንደሚፈጥር አመልክታለች። ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የማምረት አቅሟን እያስፋፋች መሆኗን፣ እንዲሁም በማዕድናት፣ በታዳሽ ኢነርጂ እና እያደገ ባለው የኢንዱስትሪ አቅም ላይ አጋርነቶችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ትልቅ ዕድል መሆኑን፣ ለጎረቤት ሀገራት የሚደረገው የኃይል አቅርቦት እና አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ መሆኗ ለአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ትስስር ያላትን አበርክቶ በግልጽ በማስመዝገብ መድረኩን ተጠቃማበታለች። ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እያከናወነችና የውጭ ዕዳዋን ለማሸጋሸግ እየሰራች መሆኗን ገልጻ፤ በፈተና ውስጥ ለሚገኙ ኢኮኖሚዎች የዕዳ አከፋፈል ሂደት ፈጣን፣ ግልጽ እና ተገማች መሆን እንዳለበት አሳስባለች። እንዲሁም በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ያላቸው ውክልና ፍትሃዊ፣ ተደማጭነታቸውን ያረጋገጠ እና ተጨባጭ ውጤት የሚያመጣ መሆን እንዳለበት ጠንካራ ጥሪ አቅርባለች። በጉባኤው ባደረገችው ንቁ ተሳትፎም ሀገራችን የዓለም ንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን፣ በዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ምክር ቤት ተጨማሪ መቀመጫ እንድታገኝ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) በአዲስ አበባ እንድታዘጋጅ ድጋፍ አግኝታለች፤ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (NDB) ቢሮ በአዲስ አበባ እንዲከፈት እና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ወደ ስምምነት የሚቀይር «የብሪክስ አስተባባሪ» እንዲቋቋም ያቀረበቻቸው ምክረ ሀሳቦች ሰፊ ተቀባይነት አግኝተዋል። ከብሪክስ መድረክ ጎን ለጎን ከተከናወኑ ሰፊ የዲፕሎማሲ ሥራዎች መካከል ከዓለም መሪዎች ጋር የተደረጉት ውይይቶች ሀገራዊ ጥቅሞችን ከማስጠበቅና አጋርነትን ከማጠናከር አንፃር ትልቅ ስኬት የተመዘገበባቸው ነበሩ። ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በኢትዮጵያና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት ተደርጓል። ውይይቱ በመከላከያና ደኅንነት፣ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እንዲሁም በባህልና ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት መስኮች ያለውን ትብብር ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነት የተረጋገጠበት ነበር። በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረገው ዝግጅት፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብራችንን ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት መፍጠር ተችሏል። ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋርም በመከላከያ ትብብር ማሳደግ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በአቅም ግንባታ እና በማዕድን ልማት ዙሪያ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤ የዘመናት ታሪካዊ ትስስራችንን ወደተግባራዊ የኢኮኖሚና ልማት ምዕራፍ ማሸጋገር ተችሏል። በተጨማሪም ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ጋር በኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝም፣ የታዳሽ ኃይል አጋርነትና በአምራች ዘርፍ ተሞክሮዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጎ ለሀገር ውስጥ ልማት የሚሆን ትልቅ በር ተከፍቷል። ከአቡ ዳቢ አልጋ ወራሽ ልዑል ሼህ ኻሊድ ቢን ሙሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር በብሪክስ ቅድመ-አጀንዳዎችና በሁለገብ ትብብር ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ጋርም በቀይ ባሕር አካባቢ ወቅታዊ ሁነቶች እና በቀጣናው የደኅንነት መረጋጋት እንዲሁም በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ የንግድ፣ የኢኮኖሚና ልማት ልውውጦቻችንን ይበልጥ ለማስፋፋት በጋራ ለመሥራት ስምምነት ላይ ተደርሷል። በአጠቃላይ፣ ኢትዮጵያ በ18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ያከናወነቻቸው ስትራቴጂካዊ የዲፕሎማሲ ሥራዎችና ያስመዘገበቻቸው ተጨባጭ ውጤቶች የሀገሪቱን የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን እውን የሚያደርጉ ወሳኝ ምሶሶዎች ናቸው። መንግሥት በዚህ ታሪካዊ መድረክ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነቷን በመጠቀም ስትራቴጂካዊ ጥቅሟን በድፍረት የምትጠይቅ፤ ለአፍሪካ ልማት፣ ሰላም እና ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ ትብብር የቆመች አስተማማኝ አጋር መሆኗን በተግባር አስመስክሯል። የኢትዮጵያ ማንሰራራት የአፍሪካን ሕዳሴ ያበስራል!
በቀጣናው ያሉ ፈተናዎችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራት የጋራ ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው - ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Sep 15, 2026 345
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ በቀጣናው እያጋጠሙ የሚገኙ ፈተናዎች በዘላቂነት እንዲፈቱ የአባል ሀገራት አብሮነትና የጋራ ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢጋድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት 74ኛው አስቸኳይ ስብሰባውን ዛሬ በጅቡቲ አካሂዷል። በስብሰባው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች ተሳትፈዋል። በቀጣናው ሰላም እና ጸጥታ እንዲሁም በሌሎች አበይት ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጓል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በቀጣናው እያጋጠሙ ያሉ ፈተናዎችን በዘላቂነት ለመቋቋም የአባል ሀገራት አብሮነትና የጋራ ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው።   በኢጋድ ሴክሬታሪያት በኩል የተከናወኑ የልማትና የሰላም ሥራዎች አበረታች ውጤቶችን እያስገኙ መሆናቸውን በመግለጽ፣ ተቋሙ ለቀጣናው ህዝቦች ብልጽግና መረጋገጥ የጸና አቋም እንዳለው አመልክተዋል። ምንም እንኳን የተለያዩ ጂኦፖለቲካዊ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ የኢጋድ ሴክሬታሪያት ያለፉት ስድስት ወራት አፈጻጸም አበረታች የሚባል መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣናዊ መሠረተ ልማት እና የጤና ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ያነሱት ዋና ፀሐፊው፤ የቀጣናው የከርሰ ምድር ውሃ መረጃ ሥርዓት የአገልግሎት ተደራሽነት የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ጠቁመዋል። እንዲሁም የቀጣናው ዓለም አቀፍ የጤና ሽፋን መረጃ ጠቋሚ (ኢንዴክስ) ከ60 ወደ 65 በመቶ ከፍ ማለቱንና ይህም እ.አ.አ በ2027 70 በመቶ ለማድረስ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን ነው ያነሱት። በሌላ በኩል ሱዳን ወደ ኢጋድ ሙሉ አባልነቷ መመለሷ የቀጣናውን ትብብርና አንድነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው እ.አ.አ ጁላይ 2026 ወደ ሱዳን ባቀኑበት ወቅት የኢጋድ የሱዳን ልዑክ ቢሮ በድጋሚ በይፋ መከፈቱን አስታውሰው ይህ እርምጃ ከቀጣናው ሕዝቦች ጋር ያለውን ቀጥተኛና ዘላቂ ትስስር አጠናክሮ የሚያስቀጥል መሆኑን አመላክተዋል። ኢጋድ ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኤጀንሲዎች እና ከሌሎች ስትራቴጂካዊ አጋሮች ጋር ያለው ግንኙነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ወሳኝ ነው ብለዋል። አጋርነቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን አቅም በማጠናከር ረገድ የጎላ ድርሻ እንደሚያበረክትም ነው ያነሱት። በቀጣይ ሊከሰቱ የሚችሉ የአየር ንብረት ለውጥ አደጋዎችን የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን በማጠናከር ለመቋቋም የሚያስችሉ አሰራሮች እየተቀረፁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሀገራት የኤልኒኖ (El Niño) የአየር ንብረት መዛባት የሚያስከትለውን ስጋት ለመቀነስ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንዳለባቸው አሳስበዋል። በሌላ በኩል ቀጣናውን ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር ለማስተሳሰርና በቴክኖሎጂ የታገዘ የልማት መሠረት ለመጣል የተጀመሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ገልጸዋል። ስብሰባው የቀጣናውን ሰላም፣ ደህንነት እና ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን በሚያስችሉ ሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከርና ውሳኔዎችን በማሳለፍ መጠናቀቁን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የኢጋድ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ከተቋሙ ቁልፍ የፖሊሲ አደረጃጀቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ የድርጅቱን ሥራዎች በመምራትና በአባል ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና የሚጫወት ነው።
በተለያየ መንገድ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ ቅርሶች እንዲመለሱ እየተደረገ ነው
Sep 15, 2026 365
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):-በተለያየ መንገድ ከኢትዮጵያ ተዘርፈው የተወሰዱ ቅርሶች ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ገለጸ። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከአሜሪካ የተመለሱና የተረከባቸውን 17 የብራና መጻሕፍት ለሰባት የተለያዩ ተቋማት አስረክቧል።   በሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው እንዳሉት፤ ለቅርስ ማስመለስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በተለያዩ ጊዜያትና መንገዶች ወጥተው የነበሩ ቅርሶች እንዲመለሱ ተደርገዋል።   ዛሬ ወደ ሀገር የተመለሱት 17 የብራና መጻሕፍት የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያን በቅርበት የሚያውቁት ጄራልድ ዌይነር የተባሉ ግለሰብ የብራና መጻሕፍቱን በአሜሪካ ከሚገኙ የጥንታዊ ዕቃዎች ገበያ በተለያዩ ጊዜያት በመግዛት በግል ስብስበው ማቆየታቸውንም አስታውሰዋል። ጄራልድ ዌይነር ከሞቱ በኋላ ባለቤታቸው ባርበራ ዌይነር ቅርሶቹ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ አለባቸው በማለታቸውና በተደረገው ንግግር ቅርሶቹን ማስመለስ ተችሏል ብለዋል። እነዚህ ከ13ኛው እስከ 18ኛው ክፍለ ዘመን ዕድሜ ያላቸው 17 የብራና መጻሕፍት ለሰባት ተቋማት መሰራጨታቸውንም ገልጸዋል። በቀጣይም ሌሎች ቅርሶችን የማስመለስ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በርካታ የኢትዮጵያ ቅርሶች ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚገቡ አመልክተዋል። በተጨማሪም በአቡዳቢ ለጨረታ የወጣውን የአፄ ቴዎድሮስ ብራና ከጨረታ እንዲወጣና ወደ ኢትዮጵያ ለማስመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤልያስ ሽኩር በበኩላቸው፤ ከኢትዮጵያ ወጥተው የነበሩ የተለያዩ ጥንታዊ ቅርሶችና መጻሕፍት ከተለያዩ አካላት ተሰብስበው እንዲመለሱ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።   በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ67 በላይ ቅርሶችን ማስመለስ መቻሉንና ዛሬ የተመለሱት የብራና መጻሕፍት የኢትዮጵያ የረጅም ዘመን የእውቀት ታሪክ ምስክሮች መሆናቸውን ጠቁመዋል።   የቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ አባል ዶክተር አሉላ ፓንክርስት በበኩላቸው፤ እነዚህ 17 የብራና መጻሕፍት በአንድ ላይ መመለሳቸው ሁነቱን የተለየ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።   ቅርሱን ወደ ኢትዮጵያ ይዞ የመጣው ቡድን ወኪል ፕሮፌሰር ስቲቭ ዴላማተር በበኩላቸው፤ እያንዳንዱ የጽሑፍ ቅጅ የራሱ የሆነ ታሪካዊ እሴት ያለው በመሆኑ፣ እነዚህን ውድ ቅርሶች አክብሮት ባለው መልኩ መመለስ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ማንሰራራት የአፍሪካን ሕዳሴ ያበስራል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Sep 15, 2026 410
ኢትዮጵያ አዲሱን ዓመት ብሔራዊ ጥቅሞቿን በማስቀደምና የአፍሪካውያን እውነተኛ ድምፅ በመሆን ጀምራዋለች። በዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ የጂኦፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ጽኑና ገለልተኛ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን በመከተል የብሪክስ አባል መሆን የቻለችው ኢትዮጵያ፣ በሕንድ ኒው ዴልሂ በተካሄደው 18ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ ላይ አህጉራዊ አርአያነቷንና ስትራቴጂካዊ ተሰሚነቷን በተግባር አስመስክራለች። “ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት” በሚል መሪ ቃል የተካሄደው ይህ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ ከአባልና አጋር ሀገራት ጋር ያላትን ሁለገብ ትስስር ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገረና ፍትሃዊና አካታች ዓለም አቀፍ ሥርዓት እንዲገነባ ያላትን ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ምዕራፍ ሆኗል።   ኢትዮጵያ በጉባኤው መድረክ ላይ ባነጸባረቀችው አቋም፣ ሀገራት ቀውሶች ከመከሰታቸው በፊት የመቋቋም አቅም ሊገነቡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥታለች። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ባደረገችው ጥረት ከውጭ ለእርዳታ ከሚገባ የስንዴ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ መላቀቋን ይፋ ያደረገች ሲሆን የብሪክስ የሰብል ልውውጥ ማዕቀፍ (BRICS Grain Exchange) እንደ አምራችም ሆነ አቅራቢ ሆና ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። በመድረኩ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂና ፈጠራ ዘርፍ የዲጂታል መሠረተ ልማት፣ ዲጂታል መታወቂያ፣ የክፍያ ሥርዓቶች እና አስተማማኝ የመረጃ ልውውጥ አውታሮችን በስፋት እየገነባች መሆኗን አስገንዝባለች። ለአፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት ለመምራት የሚያስችለውን «የመደመር ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ» እያቋቋመች መሆኗን በመግለጽ፣ ከብሪክስ ተቋማት ጋር በጋራ ለመሥራት ያላትን ዝግጁነት አረጋግጣለች።   አፍሪካ የበርካታ ማዕድናት ሀብት ባለቤት መሆኗን በማስታወስም፣ የማዕድን ሀብት ለኢነርጂ ሽግግር፣ ለላቀ ማኑፋክቸሪንግ እና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ወሳኝ መሆኑን ኢትዮጵያ አንጸባርቃለች። የብሪክስ አባል ሀገራት የካፒታል፣ የቴክኖሎጂ እና የገበያ አማራጭ በመያዛቸው እነዚህን ሀብቶች አቀናጅቶ ለመጠቀምና በጥሬ ሀብቱ ላይ እሴት ለመጨመር ትልቅ እድል እንደሚፈጥር አመልክታለች። ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የማምረት አቅሟን እያስፋፋች መሆኗን፣ እንዲሁም በማዕድናት፣ በታዳሽ ኢነርጂ እና እያደገ ባለው የኢንዱስትሪ አቅም ላይ አጋርነቶችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ትልቅ ዕድል መሆኑን፣ ለጎረቤት ሀገራት የሚደረገው የኃይል አቅርቦት እና አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ መሆኗ ለአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ትስስር ያላትን አበርክቶ በግልጽ በማስመዝገብ መድረኩን ተጠቃማበታለች። ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እያከናወነችና የውጭ ዕዳዋን ለማሸጋሸግ እየሰራች መሆኗን ገልጻ፤ በፈተና ውስጥ ለሚገኙ ኢኮኖሚዎች የዕዳ አከፋፈል ሂደት ፈጣን፣ ግልጽ እና ተገማች መሆን እንዳለበት አሳስባለች። እንዲሁም በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ያላቸው ውክልና ፍትሃዊ፣ ተደማጭነታቸውን ያረጋገጠ እና ተጨባጭ ውጤት የሚያመጣ መሆን እንዳለበት ጠንካራ ጥሪ አቅርባለች። በጉባኤው ባደረገችው ንቁ ተሳትፎም ሀገራችን የዓለም ንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን፣ በዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ምክር ቤት ተጨማሪ መቀመጫ እንድታገኝ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) በአዲስ አበባ እንድታዘጋጅ ድጋፍ አግኝታለች፤ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (NDB) ቢሮ በአዲስ አበባ እንዲከፈት እና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ወደ ስምምነት የሚቀይር «የብሪክስ አስተባባሪ» እንዲቋቋም ያቀረበቻቸው ምክረ ሀሳቦች ሰፊ ተቀባይነት አግኝተዋል። ከብሪክስ መድረክ ጎን ለጎን ከተከናወኑ ሰፊ የዲፕሎማሲ ሥራዎች መካከል ከዓለም መሪዎች ጋር የተደረጉት ውይይቶች ሀገራዊ ጥቅሞችን ከማስጠበቅና አጋርነትን ከማጠናከር አንፃር ትልቅ ስኬት የተመዘገበባቸው ነበሩ። ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በኢትዮጵያና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት ተደርጓል። ውይይቱ በመከላከያና ደኅንነት፣ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እንዲሁም በባህልና ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት መስኮች ያለውን ትብብር ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነት የተረጋገጠበት ነበር። በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረገው ዝግጅት፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብራችንን ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት መፍጠር ተችሏል። ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋርም በመከላከያ ትብብር ማሳደግ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በአቅም ግንባታ እና በማዕድን ልማት ዙሪያ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤ የዘመናት ታሪካዊ ትስስራችንን ወደተግባራዊ የኢኮኖሚና ልማት ምዕራፍ ማሸጋገር ተችሏል። በተጨማሪም ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ጋር በኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝም፣ የታዳሽ ኃይል አጋርነትና በአምራች ዘርፍ ተሞክሮዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጎ ለሀገር ውስጥ ልማት የሚሆን ትልቅ በር ተከፍቷል። ከአቡ ዳቢ አልጋ ወራሽ ልዑል ሼህ ኻሊድ ቢን ሙሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር በብሪክስ ቅድመ-አጀንዳዎችና በሁለገብ ትብብር ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ጋርም በቀይ ባሕር አካባቢ ወቅታዊ ሁነቶች እና በቀጣናው የደኅንነት መረጋጋት እንዲሁም በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ የንግድ፣ የኢኮኖሚና ልማት ልውውጦቻችንን ይበልጥ ለማስፋፋት በጋራ ለመሥራት ስምምነት ላይ ተደርሷል። በአጠቃላይ፣ ኢትዮጵያ በ18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ያከናወነቻቸው ስትራቴጂካዊ የዲፕሎማሲ ሥራዎችና ያስመዘገበቻቸው ተጨባጭ ውጤቶች የሀገሪቱን የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን እውን የሚያደርጉ ወሳኝ ምሶሶዎች ናቸው። መንግሥት በዚህ ታሪካዊ መድረክ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነቷን በመጠቀም ስትራቴጂካዊ ጥቅሟን በድፍረት የምትጠይቅ፤ ለአፍሪካ ልማት፣ ሰላም እና ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ ትብብር የቆመች አስተማማኝ አጋር መሆኗን በተግባር አስመስክሯል። የኢትዮጵያ ማንሰራራት የአፍሪካን ሕዳሴ ያበስራል!
በመደመር መንግሥት በሳል ዲፕሎማሲ ዓቅም የተመዘገበ የብሪክስ ድል
Sep 15, 2026 380
ኢትዮጵያ በረጅም የዲፕሎማሲ ታሪኳ የገነባችውን ልምድ ከዘመኑ ዓለም አቀፍ ለውጦች ጋር በማጣጣም፣ብሔራዊ ጥቅሟን በማስቀደምና ከተለያዩ የዓለም ኃይሎች ጋር አጋርነቷን በማስፋት በሳል የውጭ ግንኙነት አካሄድ እየተከተለች ትገኛለች። የዚህ አካሄድ ጉልህ ውጤት ማሳያ ደግሞ ኢትዮጵያ የብሪክስን ጥምረት መቀላቀሏ ነው። ይህ ስኬት ግን የጥምረቱ አባል በመሆኗ ብቻ የሚያበቃ አይደለም። ኢትዮጵያ በመድረኩ የራሷን ብሔራዊ አጀንዳ በጥምረቱ የጋራ አቋም እንዲያገኝ ማድረግ መቻሏ ዋናው የዲፕሎማሲ ውጤት ሆኗል። ይህን የዲፕሎማሲ አቅጣጫ በመቅረጽና በመምራት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚና ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ የብሪክስ ቡድንን ለመቀላቀል ፍላጎቷን በመግለጽ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ቀጥተኛ እና ታሪካዊ የዲፕሎማሲ መሪነት በነሐሴ 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ በነበረው 15ተኛው የብሪክስ ጉባዔ ላይ ጥያቄዋ ተቀባይነትን አግኝቶ፣ በጥር 2016 ዓ.ም በይፋ መቀላቀሏ ይታወሳል፡፡ አሁን ላይ ከ11 የብሪክስ አባል ሀገራት ውስጥ አንዷ ሆና በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ የራሷን ጉልህ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በተለዋዋጭ የዓለም ሥርዓት ውስጥ ከአንድ የኃይል ጎራ ጋር ብቻ ሳትወግን ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የትብብር መድረኮች ጋር በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ ግንኙነት መፍጠር እንዳለባት ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት ዓለም አቀፍ የትብብርና የተፅዕኖ አድማሷን እያሰፋች ነው። የብሪክስ አባልነትም ከዚህ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫ የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በብሪክስ ውስጥ መግባቷ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ጥቅም የሚያመጣውን አቅም በመለየት፣ አጀንዳውን ከኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ብሔራዊ ጥቅም ጋር የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ የዕይታ ለውጥ ውጤት ነው። ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ከዲፕሎማሲያዊ ጥረት በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቻይና፣ ከሩሲያ ከሕንድና ከሌሎች የብሪክስ አባል ሀገራት መሪዎች ጋር ባደረጉት ከፍተኛ የመሪዎች ዲፕሎማሲና ኢትዮጵያ ለዓለም ያበረከተችውን ታሪካዊ ሚና በቀጥታ ማስረዳታቸው ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ኢትዮጵያ በብሪክስ ያላት የነቃ ተሳትፎና የድል የጉዞ አሁንም ቀጥሏል። ከመስከረም 2 ቀን 2019 ዓ.ም ጀምሮ በህንድ በተካሄደው 18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ አጀንዳዎቿን አሰምታለች። ብሔራዊ መሻቷን ገልጻለች። ድሎችን ተቀዳጅታለች።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጉባኤው ባደረጉት ንግግር ለችግሮች የማይበገር ፅኑ ሥርዓት እየገነባች መሆኗን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በምግብ ሉዓላዊነት በስንዴ ምርት ያስመዘገበችውን ስኬት፣ በጤና፣ በዲጂታል ሽግግርና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ያላትን አቅም በማሳደግ ራሷን የመቻልና ለወደፊት የመዘጋጀት አቅሟን እያጠናከረች መሆኗን ጠቁመዋል። ‎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ እያደገ ካለው ገዙፍ ኢኮኖሚዋና የህዝቧ ፍላጎት አኳያ አጣዳፊ ምላሽ የሚሻ ስትራቴጂያዊ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳ መሆኑን በግልጽ አቅርበዋል። ይህ ኢትዮጵያ የራሷን ወሳኝ ብሔራዊ ጥያቄዎች በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ሁሉ በተቀናጀ መልኩ ለማስገንዘብና ምላሽ እንዲያገኙ የምትከተለውን የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ፍሬያማነት ያሳያል። ‎የመሪዎቹ ጉባኤ 140 የጋራ አቋሞችን የያዘ የኒው ዴልሂ መግለጫ በማውጣት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያም በድል ተመልሳለች። ‎‎በብሪክስ ኒው ዴልሂ የአቋም መግለጫ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የንግድ ድርጅት ለመቀላቀል የምታደርገውን ጥረት ጥምረቱ በጽኑ እንደሚደግፍ በድጋሚ አረጋግጧል።   በዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ምክር ቤት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት ብቸኛ እጩ በመሆን ተጨማሪ መቀመጫ እንድታገኝ የሚደረገውን ጥረት በጽኑ እንደሚደግፍም አመላክቷል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ኮፕ 32 ለማዘጋጀት የጀመረችውን ተነሳሽነትና ዝግጅት እንደሚደግፉ የብሪክስ አባል ሀገራት መሪዎች በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል። ‎በነገራችን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህነዱ የብሪክስ ጉባኤ ከአባልና አጋር ሀገራት መሪዎች ጋር በሁለትዮሽ የሀገራቱ ትብብር ዙሪያ ፍሬያማ ውይይቶችን ያካሄዱ ሲሆን፤ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ መስኮችና በዲጂታላይዜሽን ዙሪያ ሊኖሩ ስለሚችሉ ትብብሮች በጥልቀት መወያየታቸው ሌላኛው ስኬት ነው። ‌‎የብሪክስ አባልነት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድልም ነው። በተያያዘም የብሪክስ አባል በመሆኗ አሁን ላይ ተሰሚነቷ ከማደጉም በላይ በፋይናንስ፣ ኢንቨስትመንት እና መሰል የዕድገት መሰረተ ልማት ትብብሮች ላይ አማራጮችን አበርክቶላታል።   ለዚህም ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን በአባልነት መቀላቀሏ ለሀገራዊ የልማት ፋይናንስ፣ ለመሠረተ ልማት ድጋፍ እና ለማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን ለማግኘት የሚያስችላትና ከደቡብ ደቡብ የፋይናንስ ሥርዓቶች ጋር የሚኖራትን ትስስር የሚያጠናክር ነው። ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም በተለያዩ የብሪክስ የወጣቶች ማዕቀፍ ውስጥ በስራ ፈጠራ፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ ሳይንስ እና መሰል መስኮች ላይ በንቃት እየተሳተፉ የሚገኝ ሲሆን፣ እየተፈጠሩ በሚገኙ የኢንቨስትመንት እድሎችም በርካታ የስራ እድሎች እየተፈጠረለቸው ይገኛል፡፡ በተጨማሪም ከአባል እና አጋር ሀገራቱ ወጣቶች ጋር ትስስር የመፍጠርና ልምድ ልውውጥ የማድረግ ዕድሎችን አስገኝቶላቸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የባንኩ የአፍሪካ ቢሮ በአዲስ አበባ እንዲቋቋም ያላትን ዝግጁነት መግለጿም የብሪክስን አባልነት ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ትስስር ለመቀየር ያላትን ፍላጎት ያሳያል። የኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነት ስኬታማ ጉዞ በዓለም አቀፍ ለውጥ መካከል በተለያዩ የትብብር መድረኮች በመሳተፍ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስገኘት በትጋትና በተፅዕኖ ፈጣሪነት እየሰራች መሆኗን ያሳያል። ብሪክስ የኢትዮጵያ ጥያቄዎች የሚሰሙበት፣ አጋርነቶችን የምትገነባበት፣ ብሔራዊ ጥቅምን በማስከበር ዓለም አቀፍ ተፅዕኖ የምትፈጥርበት፣ አፍሪካን በመወከል አጀንዳዎቿን የምታራምድበት መድረክም ሆኗል።
የኢጋድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባውን ዛሬ ያካሂዳል
Sep 15, 2026 452
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት 74ኛው አስቸኳይ ስብሰባውን ዛሬ በጅቡቲ ያደርጋል። በስብሰባው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች ይሳተፋሉ። በስብሰባው አባል ሀገራት በቀጣናው ያለውን የጸጥታና የደህንነት ሁኔታ እና እየተከናወኑ ያሉ ቀጣናዊ ጥረቶችን በመገምገም ለሰላም፣ መረጋጋትና ትብብር ያላቸውን የጋራ አቋም እንዲያጠናክሩ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።   በተጨማሪም ምክር ቤቱ የድርጅቱን ተልዕኮ እና በቀጣናው ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍ እና የኢጋድ ስምምነትን (IGAD Treaty) ተፈጻሚነት ማጠናከርን ጨምሮ በዋና ዋና ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል። ስብሰባው የኢጋድ አባል ሀገራት በቀጣናው የሚገኙ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመቅረፍ እንዲሁም ለሕዝቦቻቸው ሰላም፣ መረጋጋትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡበት እንደሆነም ተገልጿል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከኢጋድ ቁልፍ የፖሊሲ አደረጃጀቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ የድርጅቱን ሥራዎች በመምራትና በአባል ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና የሚጫወት ነው።
በማእከላዊ ጎንደር ዞን የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር ሆነው እየሰሩ ነው
Sep 14, 2026 630
ጎንደር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፡- በማእከላዊ ጎንደር ዞን የመንግስትን የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር ሆነው እየሰሩ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። በአማራ ክልል የማዕከላዊ ጎንደር ዞን "አርቆ ማየት፣ አልቆ መሥራት" በሚል መሪ ቃል ያለፈው በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አወቀ አስፈሬ፤ በበጀት ዓመቱ በተለይም በሰላምና ፀጥታ ዙሪያ ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በፀጥታ አካላት የተከናወኑ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል ብለዋል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ ገብተው የነበሩ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተቀብለው እንዲመጡ መደረጉን አንስተው በርካቶች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ህብረተሰቡን በመቀላቀል የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር ሆነው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የቀድሞ ታጣቂዎቹ በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ በመሰማራት የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ህይወት ለመለወጥ ብሎም የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ እየሰሩ ይገኛሉ ብለዋል። በአስተዳደሩ በኩል አስፈላጊው እገዛ እየተደረገ መሆኑን አንስተው ሌሎችም ጫካ የሚገኙ ታጣቂዎች የጥፋትን መንገድ ትተው የሰላምን አማራጭ በመቀበል ህዝባቸውን እንዲቀላቀሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በዞኑ ከሰላምና ፀጥታ ባሻገር በግብርና፣ በኢንዱስትሪ በማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም በመሰረተ ልማት ግንባታ ዙሪያ አበረታች ውጤቶች መታየታቸውን ገልጸዋል። በዞኑ 22 ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ለአዲሱ የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጋቸውን ጠቁመው፤ በግንባታ ላይ የሚገኙ 44 ትምህርት ቤቶችን ለማጠናቀቅም በትጋት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።   በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፋሲል ሰንደቁ፤ ባለፈው በጀት ዓመት 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በስኬት ማጠናቀቅ መቻሉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ተናግረዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሴቶችና ሕፃናት ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ቀኑ ቢያድጎ በበኩላቸው፤ የሴቶችን፣ ወጣቶችንና የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል ነው ያሉት። በ2019 በጀት ዓመትም ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ የልማት ሥራዎችን ለማከናወን መታቀዱን አስረድተዋል። ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚካሄደው የውይይት መድረክ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደሮች አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው።  
በሪፎርም ሥራዎች የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሁለንተናዊ ማንሠራራት ማሸጋገር አስችለዋል
Sep 14, 2026 684
አዲስ አበባ፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፡- ባለፉት ዓመታት በሪፎርም ሥራዎች የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሁለንተናዊ ማንሠራራት ማሸጋገር ያስቻሉ መሆናቸውን የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት "በማንሠራራት ወደ ልዕልና" በሚል የፓናል ውይይት መድረክ አካሂዷል።   በፓናል ውይይቱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ አዝመራው አንደሞ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ፣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ ተገኝተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት 2018 ዓ.ም የሀገሪቱ የማንሠራራት አቅም በተጨባጭ የታየበትና ፈተናዎች ወደ ዕድል እና ስኬት የተቀየሩበት ዓመት ነበር። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁ ለሀገሪቱም ሆነ ለአፍሪካ ትልቅ አብነት መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ በየዘርፉ የተመዘገቡ አመርቂ ውጤቶች ኢትዮጵያውያን የጽናት እና የአይበገሬነት ተምሳሌት መሆናቸውን በተግባር ያስመሰከሩበት እንደነበርም አክለዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በስኬት መጠናቀቁም ትውልዱ በታሪክ ሲዘክረው የሚኖር ድል መሆኑን አብራርተዋል።   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራው አንደሞ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያን በነፃነት ሀሳብ ከማመንጨት እስከ ማደራጀት፣ ማቀናጀትና ለሀገር የሚጠቅሙ ምክረ-ሀሳቦችን ለማመንጨት የሄዱበት ርቀት የተዋጣ ሀገራዊ ምክክር እንዲካሄድ አስችሏል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የማያግባቡ ጉዳዮችን በምክክር የመፍታት ባህልና ልምምድ እንዲጎለብት መሠረት መጣሉን አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት በመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ ስኬታማ የሪፎርም ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። አዲሱ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ከመቆጣጠር ይልቅ ሚዲያዎችን የሚደግፍ፣ የሚከታተልና አቅም የሚገነባ ተቋም እንዲሆን ማስቻሉንም ጨምረው አብራርተዋል። የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በተለይ የመገናኛ ብዙኃንን አቅም በመደገፍ ረገድ ውጤታማ ሥራ እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም አዲስ የልህቀት ማዕከል በማቋቋም ጭምር በተለይ የባለሙያዎችን የዘርፍ ጋዜጠኝነት አቅም ለማዳበር እየሠራ ስለመሆኑም ተናግረዋል። በዚህም የመቆጣጠርና የመደገፍ ሥራን ሚዛን አስጠብቆ በመሄድ ረገድ የተሻለ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ይህም መገናኛ ብዙኃን ብሔራዊ ጥቅምን አክብረው እንዲሠሩ በማድረግ ረገድ መሻሻሎች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ጠቅሰዋል።   የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ፤ የሀገሪቱን የማንሠራራት ሥራዎችን ወደ ላቀ ደረጃና ልዕልና ለማሸጋገር ሁለት መሠረታዊ ተግባራት እንደሚከናወኑ አንስተዋል። የመጀመሪያው ኢትዮጵያ የገባችውን ቃል የምትፈጽም ሀገር መሆኗን የሚያሳይ አወንታዊ የሀገር ምስል (Brand) መገንባት መሆኑን ጠቁመው፤ ሁለተኛው ደግሞ ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰባሰቡበትንና ቀጣይነት ያለው ስኬት መሠረት የሚጥል የጋራ ሀገራዊ ትርክት መፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል። ይህን በማሳካት ረገድ ደግሞ የመገናኛ ብዙኃንና የኮሙኒኬሽን ተቋማት ትልቅ ሚና እንዳላቸው አውስተዋል። ከዚህ አኳያ የመገናኛ ብዙኃን ዲጂታል ሚዲያን ታሳቢ ባደረገ መልኩ አሠራራቸውን በመቀየር ሕዝብን ለሀገራዊ ራዕይ ማሰባሰብ ላይ በቀጣይነት ሥራት እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል።
18ተኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ የሁለተኛ ቀናት ቆይታ
Sep 14, 2026 606
‎የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው ከመስከረም 2 /2019ዓ.ም ጀምሮ በተካሔደው 18ተኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ መሳተፋቸው ይታወሳል፤ ‎መስከረም 3 ቀን፣ 2019 ዓ.ም የጉባዔው ሁለተኛ ቀን ‘‘ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት’’ በሚል መሪ ቃል የብሪክስ አባል እና አጋር ሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች በተሳተፉበት የተካሔደ ሲሆን፣ ጥምረቱ 140 የጋራ አቋሞችን የያዘ (የኒው ዴልሂ መግለጫ) በማውጣትም የመሪዎቹ ጉባኤ ተጠናቋል። ‎የብሪክስ ኒው ዴልሂ የአቋም መግለጫ የዓለም አቀፍ አስተዳደር ማሻሻያ፣ ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ሰላም፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ትሥሥርን ያካተቱ ዐበይት ጉዳዮች ላይ የአባል ሀገራቱን የጋራ አቋም ያንጸባረቀ ሲሆን ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የንግድ ድርጅት ለመቀላቀል የምታደርገውን ጥረት ጥምረቱ በጽኑ እንደሚደግፍ በድጋሚ አረጋግጧል፤ በዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ምክር ቤት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት ብቸኛ እጩ በመሆን ተጨማሪ መቀመጫ እንድታገኝ የሚደረገውን ጥረት በጽኑ እንደሚደግፍም አመላክቷል። በተጨማሪም ሀገሪቱ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ኮፕ 32 ለማዘጋጀት የጀመረችውን ተነሳሽነትና ዝግጅት እንደሚደግፉ በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል። ጥምረቱ 19ኛውን የብሪክስ ጉባኤ በቻይና አስተባባሪነት እንዲዘጋጅም በጋራ አጽድቋል። ‎ከመሪዎቹ ጉባኤ ጎን ለጎን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከአባልና አጋር ሀገራት መሪዎች ጋር በሁለትዮሽ የሀገራቱ ትብብር ዙሪያ ፍሬያማ ውይይቶችን ያካሄዱ ሲሆን፤ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ መስኮች ትብብር፣ በዲጂታላይዜሽን ዙሪያ ሊኖሩ ስለሚችሉ ትብብሮች በጥልቀት ተወያይተዋል። ‎‎በድኅረ ጉባኤ ለመሪዎች በተደረገው የእራት ግብዣ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተለያዩ የብሪክስ አባል እና አጋር ሀገራት መሪዎች ጋር የታደሙ ሲሆን፤ የሁለት ቀናት የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤን አጠናቅቀው ተመልሰዋል። ‎ለበለጠ ወቅታዊ መረጃ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ማኅበራዊ የሚድያ ገጾች ይከታተሉ:- ድኅረ ገፅ: https://pmo.gov.et/ ‎ፌስቡክ: https://web.facebook.com/PMOEthiopia ‎ኤክስ(ትዊተር): https://x.com/PMEthiopia ‎ዩትዩብ: https://youtube.com/@officeoftheprimeminister-e1878... #PMOEthiopia
ሰላምን በማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Sep 14, 2026 643
ደሴ/ደብረ ብርሃን፤መስከረም 4/2018 (ኢዜአ)፡- በአካባቢው የተገኘውን ሰላም በማጽናት ህብረተሰቡን የልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። የደቡብ ወሎ ዞን፣ የደሴና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደሮች የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።   የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮነን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፈው በጀት ዓመት ሰላምን በማስጠበቅ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ሥራዎችን ማከናወን ተችሏል። በተለይም በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ በማዕድን ሀብት ልማት፣ በቱሪዝም፣ በኢንቨስትመንት እና በሌሎች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። በአዲሱ በጀት ዓመትም ህብረተሰቡን በማሳተፍና ሰላምን በማጽናት የተጀመረውን ብልጽግናን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋ ዳኜ በበኩላቸው፣ ባለፈው በጀት ዓመት በፓርቲና በመንግሥት ውጤታማ የሆኑ ተግባራትን ማከናወን ተችሏል። ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ምርጫ ከማካሄድ ባለፈ በሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ሥራዎችን ማከናወን መቻሉንም ለአብነት አንስተዋል።   በተመሳሳይ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ እንዳሉት፣ የከተማዋን ሰላም በመጠበቅ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬታማ የልማት ሥራዎችን ማከናወን ተችሏል።   በተለይ በኮሪደር ልማት፣ በ"ስማርት ሲቲ" ግንባታ፣ በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎችም የተመዘገቡ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። ባለፈው በጀት ዓመት በተከናወኑ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች አበረታች ውጤት መመዝገቡን የገለጹት ደግሞ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ናቸው።   በተያዘው በጀት ዓመትም የከተማዋን ሁለገብ ዕድገት ለማፋጠን የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችና ስኬቶችን በማስፋት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የልማት ሥራዎች በልዩ ትኩረት ይከናወናሉ። በዚህ በጀት ዓመት ከ23 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ እየተሠራ ሲሆን፣ ለውጤታማነቱም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ከሕዝቡ ጋር ተቀናጅተው መሥራት ይገባቸዋል ብለዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው እንዳሉት፤ በአዲሱ በጀት ዓመት የዕድገትና አሻጋሪ ዕቅድ ግቦች ስኬታማ እንዲሆኑ በትኩረት ይሠራል።   በከተማዋ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥና ልማት እንዲፋጠን የሕዝብ አንድነትን በማጠናከር የተረጋጋ ሰላም የማስፈን ሥራው ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት ።   በየከተሞቹ በሚካሄደው መድረክ የፓርቲና የመንግሥት ዕቅዶች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው ሲሆን፣ በመድረኩም የዞን ፣ የከተማ፣ የወረዳና የክፍለ ከተማ አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፦
Sep 13, 2026 1041
የመደመር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት እንድትመራ ትልቅ ሚና ይጫወታል ሀገራት ቀውሶች ከመከሰታቸው በፊት የመቋቋም አቅም ሊገነቡ ይገባል።በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ ፈተናን መቋቋም የሚያስችሉ ስርዓቶችን እየገነባች ትገኛለች መንግስት በምግብ ዋስትና ላይ ባከናወነው ተግባር ኢትዮጵያ ከውጭ ከሚገባ ስንዴ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ ወጥታ ራሷን ችላለች ኢትዮጵያ ለታቀደው የብሪክስ የሰብል ልውውጥ ማዕቀፍ (BRICS Grain Exchange) እንደ አምራችም ሆነ አቅራቢ ሆና ለመሳተፍ ዝግጁ ናት ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የሚያጋጥሙ ቀውሶችን ለመቋቋም የሀገር ውስጥ የማምረት አቅሟን እያሳደገች ነው። የፋርማሲዩቲካልና የመድኃኒት ማምረቻዎችንም እያስፋፋች ነው በቴክኖሎጂው ዘርፍ ዲጂታል መሠረተ ልማት፣ ዲጂታል መታወቂያ (Digital ID)፣ የክፍያ ሥርዓቶች እና የመረጃ ልውውጥ በስፋት እየተገነቡ ነው መረጃዎች ደህንነታቸው በተጠበቀ መልኩ በሕግ አግባብ ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ ነው።ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ይህንን ለውጥ የበለጠ ያጠናክረዋል በቀጣዩ ትውልድ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ይበልጥ ሰዎችን ማገልገል፣ ብዙ ቋንቋዎችን መረዳት እና ሰፊ የሰው ልጅ እውቀት ማካተት አለበት አፍሪካ የነገውን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን በባለቤትነት ለመምራት የምርምር፣ የኮምፒውቲንግ አቅም፣ ክህሎት እና ተቋማት ያስፈልጋሉ ኢትዮጵያ አፍሪካን የሚወክል የቴክኖሎጂ አቅም ለመገንባት ከብሪክስ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት አላት አፍሪካ የበርካታ ማዕድናት ሀብት ባለቤት ናት።የብሪክስ አባል ሀገራት ደግሞ የካፒታል፣ የቴክኖሎጂ እና የገበያ አማራጭ አላቸው ኢትዮጵያ በማዕድናት፣ በታዳሽ ኢነርጂ እና እያደገ ያለውን የኢንዱስትሪ አቅሟን መሰረት ባደረገ መልኩ አጋርነቶችን ለመፍጠር ዝግጁ ናት ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገራቱ ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ሀገራት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ያላቸው ውክልና ፍትሃዊና ውክልናውም ተጨባጭ ውጤት ማምጣት አለበት
ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ማንሰራራት የአፍሪካን ሕዳሴ ያበስራል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Sep 15, 2026 410
ኢትዮጵያ አዲሱን ዓመት ብሔራዊ ጥቅሞቿን በማስቀደምና የአፍሪካውያን እውነተኛ ድምፅ በመሆን ጀምራዋለች። በዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ የጂኦፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ጽኑና ገለልተኛ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን በመከተል የብሪክስ አባል መሆን የቻለችው ኢትዮጵያ፣ በሕንድ ኒው ዴልሂ በተካሄደው 18ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ ላይ አህጉራዊ አርአያነቷንና ስትራቴጂካዊ ተሰሚነቷን በተግባር አስመስክራለች። “ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት” በሚል መሪ ቃል የተካሄደው ይህ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ ከአባልና አጋር ሀገራት ጋር ያላትን ሁለገብ ትስስር ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገረና ፍትሃዊና አካታች ዓለም አቀፍ ሥርዓት እንዲገነባ ያላትን ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ምዕራፍ ሆኗል።   ኢትዮጵያ በጉባኤው መድረክ ላይ ባነጸባረቀችው አቋም፣ ሀገራት ቀውሶች ከመከሰታቸው በፊት የመቋቋም አቅም ሊገነቡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥታለች። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ባደረገችው ጥረት ከውጭ ለእርዳታ ከሚገባ የስንዴ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ መላቀቋን ይፋ ያደረገች ሲሆን የብሪክስ የሰብል ልውውጥ ማዕቀፍ (BRICS Grain Exchange) እንደ አምራችም ሆነ አቅራቢ ሆና ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። በመድረኩ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂና ፈጠራ ዘርፍ የዲጂታል መሠረተ ልማት፣ ዲጂታል መታወቂያ፣ የክፍያ ሥርዓቶች እና አስተማማኝ የመረጃ ልውውጥ አውታሮችን በስፋት እየገነባች መሆኗን አስገንዝባለች። ለአፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት ለመምራት የሚያስችለውን «የመደመር ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ» እያቋቋመች መሆኗን በመግለጽ፣ ከብሪክስ ተቋማት ጋር በጋራ ለመሥራት ያላትን ዝግጁነት አረጋግጣለች።   አፍሪካ የበርካታ ማዕድናት ሀብት ባለቤት መሆኗን በማስታወስም፣ የማዕድን ሀብት ለኢነርጂ ሽግግር፣ ለላቀ ማኑፋክቸሪንግ እና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ወሳኝ መሆኑን ኢትዮጵያ አንጸባርቃለች። የብሪክስ አባል ሀገራት የካፒታል፣ የቴክኖሎጂ እና የገበያ አማራጭ በመያዛቸው እነዚህን ሀብቶች አቀናጅቶ ለመጠቀምና በጥሬ ሀብቱ ላይ እሴት ለመጨመር ትልቅ እድል እንደሚፈጥር አመልክታለች። ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የማምረት አቅሟን እያስፋፋች መሆኗን፣ እንዲሁም በማዕድናት፣ በታዳሽ ኢነርጂ እና እያደገ ባለው የኢንዱስትሪ አቅም ላይ አጋርነቶችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝ ትልቅ ዕድል መሆኑን፣ ለጎረቤት ሀገራት የሚደረገው የኃይል አቅርቦት እና አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ መሆኗ ለአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ትስስር ያላትን አበርክቶ በግልጽ በማስመዝገብ መድረኩን ተጠቃማበታለች። ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እያከናወነችና የውጭ ዕዳዋን ለማሸጋሸግ እየሰራች መሆኗን ገልጻ፤ በፈተና ውስጥ ለሚገኙ ኢኮኖሚዎች የዕዳ አከፋፈል ሂደት ፈጣን፣ ግልጽ እና ተገማች መሆን እንዳለበት አሳስባለች። እንዲሁም በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ያላቸው ውክልና ፍትሃዊ፣ ተደማጭነታቸውን ያረጋገጠ እና ተጨባጭ ውጤት የሚያመጣ መሆን እንዳለበት ጠንካራ ጥሪ አቅርባለች። በጉባኤው ባደረገችው ንቁ ተሳትፎም ሀገራችን የዓለም ንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን፣ በዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ምክር ቤት ተጨማሪ መቀመጫ እንድታገኝ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) በአዲስ አበባ እንድታዘጋጅ ድጋፍ አግኝታለች፤ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (NDB) ቢሮ በአዲስ አበባ እንዲከፈት እና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ወደ ስምምነት የሚቀይር «የብሪክስ አስተባባሪ» እንዲቋቋም ያቀረበቻቸው ምክረ ሀሳቦች ሰፊ ተቀባይነት አግኝተዋል። ከብሪክስ መድረክ ጎን ለጎን ከተከናወኑ ሰፊ የዲፕሎማሲ ሥራዎች መካከል ከዓለም መሪዎች ጋር የተደረጉት ውይይቶች ሀገራዊ ጥቅሞችን ከማስጠበቅና አጋርነትን ከማጠናከር አንፃር ትልቅ ስኬት የተመዘገበባቸው ነበሩ። ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በኢትዮጵያና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት ተደርጓል። ውይይቱ በመከላከያና ደኅንነት፣ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እንዲሁም በባህልና ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት መስኮች ያለውን ትብብር ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነት የተረጋገጠበት ነበር። በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረገው ዝግጅት፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብራችንን ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት መፍጠር ተችሏል። ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋርም በመከላከያ ትብብር ማሳደግ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በአቅም ግንባታ እና በማዕድን ልማት ዙሪያ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤ የዘመናት ታሪካዊ ትስስራችንን ወደተግባራዊ የኢኮኖሚና ልማት ምዕራፍ ማሸጋገር ተችሏል። በተጨማሪም ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ጋር በኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝም፣ የታዳሽ ኃይል አጋርነትና በአምራች ዘርፍ ተሞክሮዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጎ ለሀገር ውስጥ ልማት የሚሆን ትልቅ በር ተከፍቷል። ከአቡ ዳቢ አልጋ ወራሽ ልዑል ሼህ ኻሊድ ቢን ሙሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር በብሪክስ ቅድመ-አጀንዳዎችና በሁለገብ ትብብር ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፤ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ጋርም በቀይ ባሕር አካባቢ ወቅታዊ ሁነቶች እና በቀጣናው የደኅንነት መረጋጋት እንዲሁም በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ የንግድ፣ የኢኮኖሚና ልማት ልውውጦቻችንን ይበልጥ ለማስፋፋት በጋራ ለመሥራት ስምምነት ላይ ተደርሷል። በአጠቃላይ፣ ኢትዮጵያ በ18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ያከናወነቻቸው ስትራቴጂካዊ የዲፕሎማሲ ሥራዎችና ያስመዘገበቻቸው ተጨባጭ ውጤቶች የሀገሪቱን የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን እውን የሚያደርጉ ወሳኝ ምሶሶዎች ናቸው። መንግሥት በዚህ ታሪካዊ መድረክ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነቷን በመጠቀም ስትራቴጂካዊ ጥቅሟን በድፍረት የምትጠይቅ፤ ለአፍሪካ ልማት፣ ሰላም እና ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ ትብብር የቆመች አስተማማኝ አጋር መሆኗን በተግባር አስመስክሯል። የኢትዮጵያ ማንሰራራት የአፍሪካን ሕዳሴ ያበስራል!
በመደመር መንግሥት በሳል ዲፕሎማሲ ዓቅም የተመዘገበ የብሪክስ ድል
Sep 15, 2026 380
ኢትዮጵያ በረጅም የዲፕሎማሲ ታሪኳ የገነባችውን ልምድ ከዘመኑ ዓለም አቀፍ ለውጦች ጋር በማጣጣም፣ብሔራዊ ጥቅሟን በማስቀደምና ከተለያዩ የዓለም ኃይሎች ጋር አጋርነቷን በማስፋት በሳል የውጭ ግንኙነት አካሄድ እየተከተለች ትገኛለች። የዚህ አካሄድ ጉልህ ውጤት ማሳያ ደግሞ ኢትዮጵያ የብሪክስን ጥምረት መቀላቀሏ ነው። ይህ ስኬት ግን የጥምረቱ አባል በመሆኗ ብቻ የሚያበቃ አይደለም። ኢትዮጵያ በመድረኩ የራሷን ብሔራዊ አጀንዳ በጥምረቱ የጋራ አቋም እንዲያገኝ ማድረግ መቻሏ ዋናው የዲፕሎማሲ ውጤት ሆኗል። ይህን የዲፕሎማሲ አቅጣጫ በመቅረጽና በመምራት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚና ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ የብሪክስ ቡድንን ለመቀላቀል ፍላጎቷን በመግለጽ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ቀጥተኛ እና ታሪካዊ የዲፕሎማሲ መሪነት በነሐሴ 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ በነበረው 15ተኛው የብሪክስ ጉባዔ ላይ ጥያቄዋ ተቀባይነትን አግኝቶ፣ በጥር 2016 ዓ.ም በይፋ መቀላቀሏ ይታወሳል፡፡ አሁን ላይ ከ11 የብሪክስ አባል ሀገራት ውስጥ አንዷ ሆና በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ የራሷን ጉልህ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በተለዋዋጭ የዓለም ሥርዓት ውስጥ ከአንድ የኃይል ጎራ ጋር ብቻ ሳትወግን ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የትብብር መድረኮች ጋር በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ ግንኙነት መፍጠር እንዳለባት ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት ዓለም አቀፍ የትብብርና የተፅዕኖ አድማሷን እያሰፋች ነው። የብሪክስ አባልነትም ከዚህ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫ የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በብሪክስ ውስጥ መግባቷ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ጥቅም የሚያመጣውን አቅም በመለየት፣ አጀንዳውን ከኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ብሔራዊ ጥቅም ጋር የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ የዕይታ ለውጥ ውጤት ነው። ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ከዲፕሎማሲያዊ ጥረት በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቻይና፣ ከሩሲያ ከሕንድና ከሌሎች የብሪክስ አባል ሀገራት መሪዎች ጋር ባደረጉት ከፍተኛ የመሪዎች ዲፕሎማሲና ኢትዮጵያ ለዓለም ያበረከተችውን ታሪካዊ ሚና በቀጥታ ማስረዳታቸው ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ኢትዮጵያ በብሪክስ ያላት የነቃ ተሳትፎና የድል የጉዞ አሁንም ቀጥሏል። ከመስከረም 2 ቀን 2019 ዓ.ም ጀምሮ በህንድ በተካሄደው 18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ አጀንዳዎቿን አሰምታለች። ብሔራዊ መሻቷን ገልጻለች። ድሎችን ተቀዳጅታለች።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጉባኤው ባደረጉት ንግግር ለችግሮች የማይበገር ፅኑ ሥርዓት እየገነባች መሆኗን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በምግብ ሉዓላዊነት በስንዴ ምርት ያስመዘገበችውን ስኬት፣ በጤና፣ በዲጂታል ሽግግርና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ያላትን አቅም በማሳደግ ራሷን የመቻልና ለወደፊት የመዘጋጀት አቅሟን እያጠናከረች መሆኗን ጠቁመዋል። ‎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ እያደገ ካለው ገዙፍ ኢኮኖሚዋና የህዝቧ ፍላጎት አኳያ አጣዳፊ ምላሽ የሚሻ ስትራቴጂያዊ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳ መሆኑን በግልጽ አቅርበዋል። ይህ ኢትዮጵያ የራሷን ወሳኝ ብሔራዊ ጥያቄዎች በምትሳተፍባቸው ዓለም አቀፍ መድረኮች ሁሉ በተቀናጀ መልኩ ለማስገንዘብና ምላሽ እንዲያገኙ የምትከተለውን የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ፍሬያማነት ያሳያል። ‎የመሪዎቹ ጉባኤ 140 የጋራ አቋሞችን የያዘ የኒው ዴልሂ መግለጫ በማውጣት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያም በድል ተመልሳለች። ‎‎በብሪክስ ኒው ዴልሂ የአቋም መግለጫ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የንግድ ድርጅት ለመቀላቀል የምታደርገውን ጥረት ጥምረቱ በጽኑ እንደሚደግፍ በድጋሚ አረጋግጧል።   በዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ምክር ቤት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት ብቸኛ እጩ በመሆን ተጨማሪ መቀመጫ እንድታገኝ የሚደረገውን ጥረት በጽኑ እንደሚደግፍም አመላክቷል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ኮፕ 32 ለማዘጋጀት የጀመረችውን ተነሳሽነትና ዝግጅት እንደሚደግፉ የብሪክስ አባል ሀገራት መሪዎች በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል። ‎በነገራችን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህነዱ የብሪክስ ጉባኤ ከአባልና አጋር ሀገራት መሪዎች ጋር በሁለትዮሽ የሀገራቱ ትብብር ዙሪያ ፍሬያማ ውይይቶችን ያካሄዱ ሲሆን፤ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ መስኮችና በዲጂታላይዜሽን ዙሪያ ሊኖሩ ስለሚችሉ ትብብሮች በጥልቀት መወያየታቸው ሌላኛው ስኬት ነው። ‌‎የብሪክስ አባልነት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድልም ነው። በተያያዘም የብሪክስ አባል በመሆኗ አሁን ላይ ተሰሚነቷ ከማደጉም በላይ በፋይናንስ፣ ኢንቨስትመንት እና መሰል የዕድገት መሰረተ ልማት ትብብሮች ላይ አማራጮችን አበርክቶላታል።   ለዚህም ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን በአባልነት መቀላቀሏ ለሀገራዊ የልማት ፋይናንስ፣ ለመሠረተ ልማት ድጋፍ እና ለማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን ለማግኘት የሚያስችላትና ከደቡብ ደቡብ የፋይናንስ ሥርዓቶች ጋር የሚኖራትን ትስስር የሚያጠናክር ነው። ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም በተለያዩ የብሪክስ የወጣቶች ማዕቀፍ ውስጥ በስራ ፈጠራ፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ ሳይንስ እና መሰል መስኮች ላይ በንቃት እየተሳተፉ የሚገኝ ሲሆን፣ እየተፈጠሩ በሚገኙ የኢንቨስትመንት እድሎችም በርካታ የስራ እድሎች እየተፈጠረለቸው ይገኛል፡፡ በተጨማሪም ከአባል እና አጋር ሀገራቱ ወጣቶች ጋር ትስስር የመፍጠርና ልምድ ልውውጥ የማድረግ ዕድሎችን አስገኝቶላቸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የባንኩ የአፍሪካ ቢሮ በአዲስ አበባ እንዲቋቋም ያላትን ዝግጁነት መግለጿም የብሪክስን አባልነት ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ትስስር ለመቀየር ያላትን ፍላጎት ያሳያል። የኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነት ስኬታማ ጉዞ በዓለም አቀፍ ለውጥ መካከል በተለያዩ የትብብር መድረኮች በመሳተፍ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስገኘት በትጋትና በተፅዕኖ ፈጣሪነት እየሰራች መሆኗን ያሳያል። ብሪክስ የኢትዮጵያ ጥያቄዎች የሚሰሙበት፣ አጋርነቶችን የምትገነባበት፣ ብሔራዊ ጥቅምን በማስከበር ዓለም አቀፍ ተፅዕኖ የምትፈጥርበት፣ አፍሪካን በመወከል አጀንዳዎቿን የምታራምድበት መድረክም ሆኗል።
የኢጋድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባውን ዛሬ ያካሂዳል
Sep 15, 2026 452
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት 74ኛው አስቸኳይ ስብሰባውን ዛሬ በጅቡቲ ያደርጋል። በስብሰባው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች ይሳተፋሉ። በስብሰባው አባል ሀገራት በቀጣናው ያለውን የጸጥታና የደህንነት ሁኔታ እና እየተከናወኑ ያሉ ቀጣናዊ ጥረቶችን በመገምገም ለሰላም፣ መረጋጋትና ትብብር ያላቸውን የጋራ አቋም እንዲያጠናክሩ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።   በተጨማሪም ምክር ቤቱ የድርጅቱን ተልዕኮ እና በቀጣናው ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍ እና የኢጋድ ስምምነትን (IGAD Treaty) ተፈጻሚነት ማጠናከርን ጨምሮ በዋና ዋና ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል። ስብሰባው የኢጋድ አባል ሀገራት በቀጣናው የሚገኙ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመቅረፍ እንዲሁም ለሕዝቦቻቸው ሰላም፣ መረጋጋትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡበት እንደሆነም ተገልጿል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከኢጋድ ቁልፍ የፖሊሲ አደረጃጀቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ የድርጅቱን ሥራዎች በመምራትና በአባል ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና የሚጫወት ነው።
በማእከላዊ ጎንደር ዞን የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር ሆነው እየሰሩ ነው
Sep 14, 2026 630
ጎንደር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፡- በማእከላዊ ጎንደር ዞን የመንግስትን የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር ሆነው እየሰሩ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። በአማራ ክልል የማዕከላዊ ጎንደር ዞን "አርቆ ማየት፣ አልቆ መሥራት" በሚል መሪ ቃል ያለፈው በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አወቀ አስፈሬ፤ በበጀት ዓመቱ በተለይም በሰላምና ፀጥታ ዙሪያ ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በፀጥታ አካላት የተከናወኑ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል ብለዋል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ ገብተው የነበሩ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተቀብለው እንዲመጡ መደረጉን አንስተው በርካቶች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ህብረተሰቡን በመቀላቀል የልማት አርበኛና የሰላም አምባሳደር ሆነው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የቀድሞ ታጣቂዎቹ በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ በመሰማራት የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ህይወት ለመለወጥ ብሎም የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ እየሰሩ ይገኛሉ ብለዋል። በአስተዳደሩ በኩል አስፈላጊው እገዛ እየተደረገ መሆኑን አንስተው ሌሎችም ጫካ የሚገኙ ታጣቂዎች የጥፋትን መንገድ ትተው የሰላምን አማራጭ በመቀበል ህዝባቸውን እንዲቀላቀሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በዞኑ ከሰላምና ፀጥታ ባሻገር በግብርና፣ በኢንዱስትሪ በማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም በመሰረተ ልማት ግንባታ ዙሪያ አበረታች ውጤቶች መታየታቸውን ገልጸዋል። በዞኑ 22 ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ለአዲሱ የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጋቸውን ጠቁመው፤ በግንባታ ላይ የሚገኙ 44 ትምህርት ቤቶችን ለማጠናቀቅም በትጋት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።   በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፋሲል ሰንደቁ፤ ባለፈው በጀት ዓመት 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በስኬት ማጠናቀቅ መቻሉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ተናግረዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሴቶችና ሕፃናት ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ቀኑ ቢያድጎ በበኩላቸው፤ የሴቶችን፣ ወጣቶችንና የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል ነው ያሉት። በ2019 በጀት ዓመትም ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ የልማት ሥራዎችን ለማከናወን መታቀዱን አስረድተዋል። ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚካሄደው የውይይት መድረክ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደሮች አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው።  
በሪፎርም ሥራዎች የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሁለንተናዊ ማንሠራራት ማሸጋገር አስችለዋል
Sep 14, 2026 684
አዲስ አበባ፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፡- ባለፉት ዓመታት በሪፎርም ሥራዎች የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሁለንተናዊ ማንሠራራት ማሸጋገር ያስቻሉ መሆናቸውን የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት "በማንሠራራት ወደ ልዕልና" በሚል የፓናል ውይይት መድረክ አካሂዷል።   በፓናል ውይይቱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ አዝመራው አንደሞ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ፣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ ተገኝተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት 2018 ዓ.ም የሀገሪቱ የማንሠራራት አቅም በተጨባጭ የታየበትና ፈተናዎች ወደ ዕድል እና ስኬት የተቀየሩበት ዓመት ነበር። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁ ለሀገሪቱም ሆነ ለአፍሪካ ትልቅ አብነት መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ በየዘርፉ የተመዘገቡ አመርቂ ውጤቶች ኢትዮጵያውያን የጽናት እና የአይበገሬነት ተምሳሌት መሆናቸውን በተግባር ያስመሰከሩበት እንደነበርም አክለዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በስኬት መጠናቀቁም ትውልዱ በታሪክ ሲዘክረው የሚኖር ድል መሆኑን አብራርተዋል።   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራው አንደሞ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያን በነፃነት ሀሳብ ከማመንጨት እስከ ማደራጀት፣ ማቀናጀትና ለሀገር የሚጠቅሙ ምክረ-ሀሳቦችን ለማመንጨት የሄዱበት ርቀት የተዋጣ ሀገራዊ ምክክር እንዲካሄድ አስችሏል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የማያግባቡ ጉዳዮችን በምክክር የመፍታት ባህልና ልምምድ እንዲጎለብት መሠረት መጣሉን አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት በመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ ስኬታማ የሪፎርም ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። አዲሱ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ከመቆጣጠር ይልቅ ሚዲያዎችን የሚደግፍ፣ የሚከታተልና አቅም የሚገነባ ተቋም እንዲሆን ማስቻሉንም ጨምረው አብራርተዋል። የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በተለይ የመገናኛ ብዙኃንን አቅም በመደገፍ ረገድ ውጤታማ ሥራ እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም አዲስ የልህቀት ማዕከል በማቋቋም ጭምር በተለይ የባለሙያዎችን የዘርፍ ጋዜጠኝነት አቅም ለማዳበር እየሠራ ስለመሆኑም ተናግረዋል። በዚህም የመቆጣጠርና የመደገፍ ሥራን ሚዛን አስጠብቆ በመሄድ ረገድ የተሻለ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ይህም መገናኛ ብዙኃን ብሔራዊ ጥቅምን አክብረው እንዲሠሩ በማድረግ ረገድ መሻሻሎች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ጠቅሰዋል።   የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ፤ የሀገሪቱን የማንሠራራት ሥራዎችን ወደ ላቀ ደረጃና ልዕልና ለማሸጋገር ሁለት መሠረታዊ ተግባራት እንደሚከናወኑ አንስተዋል። የመጀመሪያው ኢትዮጵያ የገባችውን ቃል የምትፈጽም ሀገር መሆኗን የሚያሳይ አወንታዊ የሀገር ምስል (Brand) መገንባት መሆኑን ጠቁመው፤ ሁለተኛው ደግሞ ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰባሰቡበትንና ቀጣይነት ያለው ስኬት መሠረት የሚጥል የጋራ ሀገራዊ ትርክት መፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል። ይህን በማሳካት ረገድ ደግሞ የመገናኛ ብዙኃንና የኮሙኒኬሽን ተቋማት ትልቅ ሚና እንዳላቸው አውስተዋል። ከዚህ አኳያ የመገናኛ ብዙኃን ዲጂታል ሚዲያን ታሳቢ ባደረገ መልኩ አሠራራቸውን በመቀየር ሕዝብን ለሀገራዊ ራዕይ ማሰባሰብ ላይ በቀጣይነት ሥራት እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል።
18ተኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ የሁለተኛ ቀናት ቆይታ
Sep 14, 2026 606
‎የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው ከመስከረም 2 /2019ዓ.ም ጀምሮ በተካሔደው 18ተኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ መሳተፋቸው ይታወሳል፤ ‎መስከረም 3 ቀን፣ 2019 ዓ.ም የጉባዔው ሁለተኛ ቀን ‘‘ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት’’ በሚል መሪ ቃል የብሪክስ አባል እና አጋር ሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች በተሳተፉበት የተካሔደ ሲሆን፣ ጥምረቱ 140 የጋራ አቋሞችን የያዘ (የኒው ዴልሂ መግለጫ) በማውጣትም የመሪዎቹ ጉባኤ ተጠናቋል። ‎የብሪክስ ኒው ዴልሂ የአቋም መግለጫ የዓለም አቀፍ አስተዳደር ማሻሻያ፣ ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ሰላም፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ትሥሥርን ያካተቱ ዐበይት ጉዳዮች ላይ የአባል ሀገራቱን የጋራ አቋም ያንጸባረቀ ሲሆን ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የንግድ ድርጅት ለመቀላቀል የምታደርገውን ጥረት ጥምረቱ በጽኑ እንደሚደግፍ በድጋሚ አረጋግጧል፤ በዓለም አቀፍ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ምክር ቤት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት ብቸኛ እጩ በመሆን ተጨማሪ መቀመጫ እንድታገኝ የሚደረገውን ጥረት በጽኑ እንደሚደግፍም አመላክቷል። በተጨማሪም ሀገሪቱ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ኮፕ 32 ለማዘጋጀት የጀመረችውን ተነሳሽነትና ዝግጅት እንደሚደግፉ በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል። ጥምረቱ 19ኛውን የብሪክስ ጉባኤ በቻይና አስተባባሪነት እንዲዘጋጅም በጋራ አጽድቋል። ‎ከመሪዎቹ ጉባኤ ጎን ለጎን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከአባልና አጋር ሀገራት መሪዎች ጋር በሁለትዮሽ የሀገራቱ ትብብር ዙሪያ ፍሬያማ ውይይቶችን ያካሄዱ ሲሆን፤ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ መስኮች ትብብር፣ በዲጂታላይዜሽን ዙሪያ ሊኖሩ ስለሚችሉ ትብብሮች በጥልቀት ተወያይተዋል። ‎‎በድኅረ ጉባኤ ለመሪዎች በተደረገው የእራት ግብዣ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተለያዩ የብሪክስ አባል እና አጋር ሀገራት መሪዎች ጋር የታደሙ ሲሆን፤ የሁለት ቀናት የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤን አጠናቅቀው ተመልሰዋል። ‎ለበለጠ ወቅታዊ መረጃ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ማኅበራዊ የሚድያ ገጾች ይከታተሉ:- ድኅረ ገፅ: https://pmo.gov.et/ ‎ፌስቡክ: https://web.facebook.com/PMOEthiopia ‎ኤክስ(ትዊተር): https://x.com/PMEthiopia ‎ዩትዩብ: https://youtube.com/@officeoftheprimeminister-e1878... #PMOEthiopia
ሰላምን በማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Sep 14, 2026 643
ደሴ/ደብረ ብርሃን፤መስከረም 4/2018 (ኢዜአ)፡- በአካባቢው የተገኘውን ሰላም በማጽናት ህብረተሰቡን የልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። የደቡብ ወሎ ዞን፣ የደሴና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደሮች የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።   የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮነን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፈው በጀት ዓመት ሰላምን በማስጠበቅ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ሥራዎችን ማከናወን ተችሏል። በተለይም በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ በማዕድን ሀብት ልማት፣ በቱሪዝም፣ በኢንቨስትመንት እና በሌሎች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። በአዲሱ በጀት ዓመትም ህብረተሰቡን በማሳተፍና ሰላምን በማጽናት የተጀመረውን ብልጽግናን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋ ዳኜ በበኩላቸው፣ ባለፈው በጀት ዓመት በፓርቲና በመንግሥት ውጤታማ የሆኑ ተግባራትን ማከናወን ተችሏል። ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ምርጫ ከማካሄድ ባለፈ በሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ሥራዎችን ማከናወን መቻሉንም ለአብነት አንስተዋል።   በተመሳሳይ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ እንዳሉት፣ የከተማዋን ሰላም በመጠበቅ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬታማ የልማት ሥራዎችን ማከናወን ተችሏል።   በተለይ በኮሪደር ልማት፣ በ"ስማርት ሲቲ" ግንባታ፣ በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎችም የተመዘገቡ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። ባለፈው በጀት ዓመት በተከናወኑ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች አበረታች ውጤት መመዝገቡን የገለጹት ደግሞ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ናቸው።   በተያዘው በጀት ዓመትም የከተማዋን ሁለገብ ዕድገት ለማፋጠን የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችና ስኬቶችን በማስፋት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የልማት ሥራዎች በልዩ ትኩረት ይከናወናሉ። በዚህ በጀት ዓመት ከ23 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ እየተሠራ ሲሆን፣ ለውጤታማነቱም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ከሕዝቡ ጋር ተቀናጅተው መሥራት ይገባቸዋል ብለዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው እንዳሉት፤ በአዲሱ በጀት ዓመት የዕድገትና አሻጋሪ ዕቅድ ግቦች ስኬታማ እንዲሆኑ በትኩረት ይሠራል።   በከተማዋ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥና ልማት እንዲፋጠን የሕዝብ አንድነትን በማጠናከር የተረጋጋ ሰላም የማስፈን ሥራው ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት ።   በየከተሞቹ በሚካሄደው መድረክ የፓርቲና የመንግሥት ዕቅዶች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው ሲሆን፣ በመድረኩም የዞን ፣ የከተማ፣ የወረዳና የክፍለ ከተማ አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፦
Sep 13, 2026 1041
የመደመር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት እንድትመራ ትልቅ ሚና ይጫወታል ሀገራት ቀውሶች ከመከሰታቸው በፊት የመቋቋም አቅም ሊገነቡ ይገባል።በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ ፈተናን መቋቋም የሚያስችሉ ስርዓቶችን እየገነባች ትገኛለች መንግስት በምግብ ዋስትና ላይ ባከናወነው ተግባር ኢትዮጵያ ከውጭ ከሚገባ ስንዴ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ ወጥታ ራሷን ችላለች ኢትዮጵያ ለታቀደው የብሪክስ የሰብል ልውውጥ ማዕቀፍ (BRICS Grain Exchange) እንደ አምራችም ሆነ አቅራቢ ሆና ለመሳተፍ ዝግጁ ናት ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የሚያጋጥሙ ቀውሶችን ለመቋቋም የሀገር ውስጥ የማምረት አቅሟን እያሳደገች ነው። የፋርማሲዩቲካልና የመድኃኒት ማምረቻዎችንም እያስፋፋች ነው በቴክኖሎጂው ዘርፍ ዲጂታል መሠረተ ልማት፣ ዲጂታል መታወቂያ (Digital ID)፣ የክፍያ ሥርዓቶች እና የመረጃ ልውውጥ በስፋት እየተገነቡ ነው መረጃዎች ደህንነታቸው በተጠበቀ መልኩ በሕግ አግባብ ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ ነው።ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ይህንን ለውጥ የበለጠ ያጠናክረዋል በቀጣዩ ትውልድ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ይበልጥ ሰዎችን ማገልገል፣ ብዙ ቋንቋዎችን መረዳት እና ሰፊ የሰው ልጅ እውቀት ማካተት አለበት አፍሪካ የነገውን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን በባለቤትነት ለመምራት የምርምር፣ የኮምፒውቲንግ አቅም፣ ክህሎት እና ተቋማት ያስፈልጋሉ ኢትዮጵያ አፍሪካን የሚወክል የቴክኖሎጂ አቅም ለመገንባት ከብሪክስ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት አላት አፍሪካ የበርካታ ማዕድናት ሀብት ባለቤት ናት።የብሪክስ አባል ሀገራት ደግሞ የካፒታል፣ የቴክኖሎጂ እና የገበያ አማራጭ አላቸው ኢትዮጵያ በማዕድናት፣ በታዳሽ ኢነርጂ እና እያደገ ያለውን የኢንዱስትሪ አቅሟን መሰረት ባደረገ መልኩ አጋርነቶችን ለመፍጠር ዝግጁ ናት ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገራቱ ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ሀገራት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ያላቸው ውክልና ፍትሃዊና ውክልናውም ተጨባጭ ውጤት ማምጣት አለበት
ማህበራዊ
የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት ነው
Sep 16, 2026 190
አዲስ አበባ፤ መስከረም 6/2019 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ መጀመርን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት በመላው ሀገሪቱ ለሚገኙ ተማሪዎች አዲሱ የትምህርት ዘመን ስኬታማ እንዲሆን ተመኝተዋል። ‎‎ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን እያንዳንዱ ተማሪ ለላቀ እውቀት በትጋትና ጉጉት ትምህርቱን መከታተልና ለጥሩ ውጤት በጽናት መትጋት እንደሚጠበቅበት ገልጸዋል። አዲሱ ትዉልድ የሀገሪቱን የወደፊት ዕድል መቅረጽ በሚያስችሉ ክህሎቶች እንዲገነባም አበረታተዋል። ‎‎በሃገሪቱ ዛሬ እየተተገበሩ የሚገኙት በርካታ የልማት ሥራዎች የነገን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ በመሆናቸው ትዉልዱ የዚህ ቀጣይ ዕድል ተጠቃሚ እና ባለአደራ መሆን ይኖርበታል ብለዋል።   የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የአዲሱ ትውልድ ቁርጠኝነት ትልቅ መሠረት መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ‎‎ብቁ እና በራሱ የሚተማመን ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመምህራኖች ትጋትና መሰጠት መሰረታዊ ምሰሶ መሆኑንም አንስተዋል። ተማሪዎችን ማነቃቃት፣ አቅማቸውን ማውጣት፣ እንዲሁም ነገ ተፎካካሪ ሆነው እንዲወጡ የሚያስችሏቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና እሴቶችን የማስታጠቅ አደራን እንዲያስቀጥሉም በትህትና አሳስበዋል። ‎‎በትምህርት ዘርፉ ውስጥ የሚገኙ ባለድርሻ አካላትም ስኬታማ እና ፍሬያማ የትምህርት ዘመን እንዲሆን የበኩላቸዉን ሃላፊነት እንዲወጡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሐረሪ ክልል በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Sep 15, 2026 320
ሐረር፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የክልሉ አመራሮች በክረምቱ ወራት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ አከናውነዋል። በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሮች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚሰጡ ችግኞች መተከላቸው ይታወሳል። በችግኝ ተከላው የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የመከላከያና ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ አርሶ አደሮች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ መሆናቸውም እንዲሁ። በዛሬው እለትም ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች 'በሃኪም' ጋራ በመገኘት የተከሏቸውን ችግኞች ውሃ የማጠጣት እና የመንከባከብ ሥራ አከናውነዋል። በክልሉ በክረምቱ ወራት የተተከሉት ችግኞች ወደ ዛፍነት እስኪቀየሩ ድረስ አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው ይገኛል። ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንዳሉት፣ በክልሉ በክረምቱ ወቅት የተተከሉት ችግኞች በአግባቡ እንዲጸድቁ አስፈላጊውን እንክብካቤ ማድረግ አስፈላጊ ነው። በአሁኑ ወቅትም በተለይ የተተከሉ ችግኞች ለሚፈለገው ዓላማ እንዲበቁ እየሰሩ የሚገኙ አካላትን አበረታተዋል። በቀጣይም ችግኞቹን ውሃ በማጠጣትና በመኮትኮት እንዲፀድቁ ማድረግ እንደሚገባም ነው ርዕሰ መስተዳድሩ ያሳሰቡት። ከዚህ በተጨማሪ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የሃኪም ጋራ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክት የስራ እንቅስቃሴን ተዘዋዉረው ተመልክተዋል።   የፕሮጀክቱ ስራ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑንም አንስተዋል።
በተለያየ መንገድ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ ቅርሶች እንዲመለሱ እየተደረገ ነው
Sep 15, 2026 365
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):-በተለያየ መንገድ ከኢትዮጵያ ተዘርፈው የተወሰዱ ቅርሶች ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ገለጸ። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከአሜሪካ የተመለሱና የተረከባቸውን 17 የብራና መጻሕፍት ለሰባት የተለያዩ ተቋማት አስረክቧል።   በሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው እንዳሉት፤ ለቅርስ ማስመለስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በተለያዩ ጊዜያትና መንገዶች ወጥተው የነበሩ ቅርሶች እንዲመለሱ ተደርገዋል።   ዛሬ ወደ ሀገር የተመለሱት 17 የብራና መጻሕፍት የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያን በቅርበት የሚያውቁት ጄራልድ ዌይነር የተባሉ ግለሰብ የብራና መጻሕፍቱን በአሜሪካ ከሚገኙ የጥንታዊ ዕቃዎች ገበያ በተለያዩ ጊዜያት በመግዛት በግል ስብስበው ማቆየታቸውንም አስታውሰዋል። ጄራልድ ዌይነር ከሞቱ በኋላ ባለቤታቸው ባርበራ ዌይነር ቅርሶቹ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ አለባቸው በማለታቸውና በተደረገው ንግግር ቅርሶቹን ማስመለስ ተችሏል ብለዋል። እነዚህ ከ13ኛው እስከ 18ኛው ክፍለ ዘመን ዕድሜ ያላቸው 17 የብራና መጻሕፍት ለሰባት ተቋማት መሰራጨታቸውንም ገልጸዋል። በቀጣይም ሌሎች ቅርሶችን የማስመለስ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በርካታ የኢትዮጵያ ቅርሶች ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚገቡ አመልክተዋል። በተጨማሪም በአቡዳቢ ለጨረታ የወጣውን የአፄ ቴዎድሮስ ብራና ከጨረታ እንዲወጣና ወደ ኢትዮጵያ ለማስመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤልያስ ሽኩር በበኩላቸው፤ ከኢትዮጵያ ወጥተው የነበሩ የተለያዩ ጥንታዊ ቅርሶችና መጻሕፍት ከተለያዩ አካላት ተሰብስበው እንዲመለሱ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።   በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ67 በላይ ቅርሶችን ማስመለስ መቻሉንና ዛሬ የተመለሱት የብራና መጻሕፍት የኢትዮጵያ የረጅም ዘመን የእውቀት ታሪክ ምስክሮች መሆናቸውን ጠቁመዋል።   የቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ አባል ዶክተር አሉላ ፓንክርስት በበኩላቸው፤ እነዚህ 17 የብራና መጻሕፍት በአንድ ላይ መመለሳቸው ሁነቱን የተለየ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።   ቅርሱን ወደ ኢትዮጵያ ይዞ የመጣው ቡድን ወኪል ፕሮፌሰር ስቲቭ ዴላማተር በበኩላቸው፤ እያንዳንዱ የጽሑፍ ቅጅ የራሱ የሆነ ታሪካዊ እሴት ያለው በመሆኑ፣ እነዚህን ውድ ቅርሶች አክብሮት ባለው መልኩ መመለስ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞኖች ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በይፋ ተጀምሯል
Sep 15, 2026 260
አምቦ/መቱ/ነቀምቴ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖች የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራው በይፋ ተጀምሯል። በክልሉ በሁሉም ደረጃዎች ከቅድመ-መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ከ10 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታ ለማስገባት ታቅዶ ሲሰራ ቆይቷል። የአዲስ እና ነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 2018 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፣ ተማሪዎች ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ወደ ክፍል እንዲገቡም በሁሉም አካባቢ ጥሪ ተደርጎ እንደነበር ይታወሳል። በምዕራብ ሸዋ፣ በኢሉ አባቦር ዞኖች እና በምስራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማም ለአዲሱ የትምህርት ዘመን አስፈላጊው ቁሳቁስ፣ የመማሪያ ክፍሎች እና የመምህራን ዝግጅት ተጠናቆ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው የተመለሱ ሲሆን፣ የመማር ማስተማር ሂደቱም በተሳካ ሁኔታ መቀጠሉ ተገልጿል። በምዕራብ ሸዋ ዞን በሚገኙ 2 ሺህ 296 የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ 858 ሺህ 856 ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ላይ በትምህርት ገበታቸው መገኘታቸውን የዞኑ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ባንዲራ ጋላና ገልጸዋል።   ሥራው ከመምህራን፣ ወላጆችና አመራሮች ጋር በተደረገ መግባባት መጀመሩና የቁሳቁስ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎችም ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተመሳሳይ የመቱ ከተማ እና የኢሉባቦር ዞን ትምህርት ጽሕፈት ቤቶች ኃላፊዎች አቶ አዳሙ ሀብቴ እና አቶ አያሌው ዘውዴ፤ ተማሪዎች በጥሩ ተነሳሽነት ትምህርት መጀመራቸውን አስታውቀዋል።   በኢሉባቦር ዞን እና በመቱ ከተማ ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ባሉ ትምህርት ቤቶች ትምህርት የተጀመረ ሲሆን፣ በመቱ ከተማ 22 ሺህ 124 እንዲሁም በዞኑ ወረዳዎች ከ211 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉ ተናግረዋል።   በመቱ ከተማ በትምህርት ገበታ ላይ ከተገኙት ተማሪዎች መካከል የ6ኛ ክፍል ተማሪ ሚኪያስ ጫላ ትምህርቱን በከፍተኛ ተነሳሽነት መከታተል መጀመሩን ተናግሯል። ዘንድሮ 6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተነ ተፈታኝ በመሆኑ ከአሁኑ ተግቶ በማጥናት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መዘጋጀቱን ገልጿል። ተማሪ አማኑኤል ግርማ በበኩሉ ትምህርቱን በአግባቡ በመከታተል ተወዳዳሪ ለመሆን ከወዲሁ መዘጋጀቱን አስታውቋል። በተመሳሳይ ዜና የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ፍቃዱ ተስጋራ (ዶ/ር) በከተማው በሚገኙ 169 ትምህርት ቤቶች ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለማስተማር ታቅዶ ወደ ሥራ ገብተናል ብለዋል።   ለትምህርት ቤት ኃላፊዎችና መምህራን ሥልጠና መስጠትን ጨምሮ ተጨማሪ ክፍሎችን የመገንባትና የመጠገን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በከተማዋ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱት ውስጥ 11 በመቶው ማለፋቸውን ተጠቅሶ፣ በዘመኑ የትምህርት ጥራትን ማሻሻልና ውጤትን ማሳደግ ዋና ትኩረት መሆኑን ገልጸዋል። በከተማው የ7ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ሳሙኤል ግርማ ትምህርቱን በአግባቡ በመከታተል የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መዘጋጀቱን ገልጿል።   ሌላኛዋ ተማሪ ለሊሴ ኦፍገአ፤ ከጅምሩ ጊዜዋን በአግባቡ በመጠቀመ መምህራኖቿን በመከታተልና በማጥናት ወጤታማ ለመሆን ማቀዷን ተናግራለች። የየአካባቢዎቹ የትምህርት ኃላፊዎችና ተማሪዎችም ዓመቱን በስኬት ለማጠናቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
የግብርና ምርት እሴት ሰንሰለትን ለማሻሻል ትብብርና የፖሊሲ ማዕቀፍ መተግበር ይገባል - ኢጋድ
Sep 15, 2026 317
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፡- በአባል ሀገራት ቀጣና የግብርና ምርትን ለማሻሻልና እሴት ለመጨመር ትብብርን በማጠናከርና ሊያግባባ የሚችል የጋራ የፖሊሲ ማዕቀፍ መተግበር እንደሚገባ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ገለጸ። ኢጋድ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ከ2026 እስከ 2035 ለ10 ዓመታት የሚተገብረውን የቀጣናው የግብርና ምርት የምግብ ሥርዓት ኢንቨስትመንት ዕቅድ የባለሙያዎች ግምገማና በሚኒስትሮች የማጽደቅ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው። የኢጋድ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አቅም ፕሮግራም አስተባባሪ ሰናይት ረጋሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢጋድ ቀጣና ሀገራት እንደ ጎርፍ፣ ድርቅና መሰል የተፈጥሮ አደጋዎችን በተደጋጋሚ የሚያስተናግዱ ናቸው። የአፍሪካ መሪዎች እ.ኤ.አ. በ2025 በዩጋንዳ ካምፓላ ተገናኝተው የምግብ ሥርዓት ግንባታ አቅም ስምምነት ሰነድ በመፈራረም ለትግበራው ቁርጠኝነታቸውን ማሳየታቸውን አስታውሰዋል።   በዚህም በአህጉር፣ በቀጣናና በሀገር ደረጃ ገቢራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ መደረጉን ገልጸው፤ የኢጋድ የግብርና ምርት የምግብ ሥርዓት ኢንቨስትመንት የ10 ዓመት ዕቅድ የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል። ከምግብ ዋስትና ጋር የተያያዙ ችግሮች በሀገር ደረጃ ብቻ የሚፈቱ አለመሆናቸውን ገልጸው፤ የ10 ዓመት ዕቅዱ የሀገራትን የጋራ ትብብር እንደሚያጠናክር ብለዋል። ለአብነት የበረሃ አንበጣ በቀጣናው ቢከሰት አንድ ሀገር ብቻውን የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አይችልም ያሉት አስተባባሪዋ፤ የቀጣናው ሀገራት በጋራ ጉዳዮች ላይ የጋራ መፍትሔና እርምጃ መውሰድ የሚችሉበትን ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ዕቅዱ ሀገራት በተናጠል ከራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት ከሚወስዷቸው የመፍትሔ አማራጮች ባለፈ ትብብራቸውን ማጠናከርና የዕውቀት ሽግግር መፍጠር እንደሚያስችልም ተናግረዋል። የኢጋድ የግብርና ምርት የምግብ ሥርዓት ኢንቨስትመንት ዕቅድ የግብርና ምርትን ከማሳደግ ባለፈ እሴት መጨመር የሚቻልበትን አቅም መገንባት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።   ድርቅ በሚከሰትበት ወቅት ቅድመ ማስጠንቀቂያ መስጠት፣ የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ፣ ድንበር ተሻጋሪ በሽታዎችን በጋራ መከላከል የሚችሉበት ሥርዓት እንዲዘረጋ ድጋፍ ማድረግ ያስችላል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ የቀጣናው ሀገራት የሚስማሙበትን እና ግብራዊ ሊያደርጉት የሚችለውን የጋራ ቀጣናዊ የፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። የግብርና ሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪና የአፍሪካ ልማት ፕሮግራም ተወካይ ዜና ሀብተወልድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከአፍሪካና ከቀጣናው ሀገራት ጋር የተናበበ ዕቅድ በመተግበር በአርዓያነት የሚጠቀስ ውጤት አስመዝግባለች ብለዋል። በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴ ልማት እንዲሁም አሁን በስፋት ግብራዊ በተደረገው የሩዝ ልማት ተጨባጭ ለውጥ መገኘቱን ገልጸዋል። ግብርና የአፍሪካ የልማት ሞተር መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ይሄንን ታሳቢ ያደረገ የግብርና ዕመርታ አምጥታለች ብለዋል። በቀጣይም ኢትዮጵያ በካምፓላ ስምምነትና በኢጋድ የ10 ዓመት የኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ በመመስረት የቀጣይ 10 ዓመት የተናበበ ዕቅድ በማውጣት ግብራዊ እንደምታደርግ ገልጸዋል። ኢጋድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለቀጣናው ሀገራት የምግብ ዋስትና መረጋገጥና በሽታ መከላከል ሥርዓት ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ ቀጣናዊ ትብብርና ተቋማዊ አንድነትን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስትራቴጂካዊ አቅምና ሙያዊ ብቃት ለመላው አፍሪካ አርአያ የሚሆን ነው 
Sep 15, 2026 287
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት አስርት ዓመታት የገነባው ስትራቴጂካዊ ዲሲፕሊን፣የቴክኒክ ልህቀት እና የላቀ ሙያዊ የብቃት ደረጃ ለመላው አፍሪካ አርአያ የሚሆን ነው ሲሉ የቀድሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ቲቦር ናጊ ገለጹ። የአየር መንገዱ ስኬት በመንግስት ባለቤትነት ብቻ የተወሰነ ሳይሆን በሙያዊ ስነምግባርና በገለልተኝነት በመመራቱ ጭምር መሆኑን የቀድሞው ዲፕሎማት ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል። ተቋሙ በቴክኒክ አቅምና በሰው ኃይል ልማት ላይ ያደረገው ሰፊ ኢንቨስትመንት አሁን ላይ ለደረሰበት ዝና እና ስኬት ቁልፍ ሚና መጫወቱን አመልክተዋል።   አየር መንገዱ ጠንካራ ስትራቴጂ ያለው እና የላቀ የቴክኒክ አቅም የተጎናጸፈ መሆኑን ገልጸው የአውሮፓ አየር መንገዶች አብራሪዎቻቸውን በአዲስ አበባ በሚገኙ ማሰልጠኛዎች (ሲሚውሌተር) ልምምድ እንዲያደርጉ እንደሚልኩ አንስተዋል። የተቋሙ መካኒኮችም በዓለም ምርጥ ከሆኑት ተርታ እንደሚመደቡ ጠቅሰው መንገደኞች ሁልጊዜም የኢትዮጵያ አየር መንገድን ተመራጭ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። ዓለም አቀፍ በረራዎች በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጠው በነበሩበት አስቸጋሪ ወቅት አየር መንገዱ የላቀ ሙያዊ ብቃት ማሳየቱን ናጊ አስታውሰዋል። በወቅቱ የቀድሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ቲቦር ናጊ በሚያገለግሉበት ወቅት፣ ሌሎች አየር ማረፊያዎች በረራቸውን ባቋረጡበት ጊዜ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት አሜሪካ ዜጎቿን ከአፍሪካ ለማስወጣት አየር መንገዱን በስፋት ስትጠቀም እንደነበር በማውሳት የአየር መንገዱን ጽናትና አይበገሬነት አንስተዋል። የቢሾፍቱን ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ያደነቁ ሲሆን ኢትዮጵያ በአፍሪካ የኢኮኖሚና የአቪዬሽን መሪነት እንድትቀጥል ይህ ፕሮጀክት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።   የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ የረጅም ጊዜ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ አርቆ አሳቢነት የተሞላበት አካሄድ ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እጅግ ከፍ ያለ ቦታ ላይ መሆኗ ለአንዳንድ አውሮፕላኖች ማረፍና መነሳት አስቸጋሪ መሆኑን በመጥቀስ፣ ይህም የፕሮጀክቱን ስትራቴጂካዊ ፋይዳ የጎላ የሚያደርገው መሆኑን ተናግረዋል። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት 12.5 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን፤ ይህ ሜጋ ፕሮጀክት በቢሾፍቱ ከተማ እየተገነባ ይገኛል። ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያን ይበልጥ የአፍሪካ ግዙፍ የአቪዬሽን ማዕከል የሚያደርጋት ነው። የኢትዮጵያን አየር መንገድ ስኬት ከረጅም ጊዜ የተቋም ጽናትና ኢንቨስትመንት ጋር የሚቆራኝ ነው ብለዋል። የቴክኒክ ባለሙያዎች ብቃት፣ስትራቴጂካዊ አስተዳደር እና የመሰረተ ልማት መቀናጀት እንዲሁም የሀገሪቱ ኢኮኖሚ እና የዓለም አቀፍ ትስስር እድገት አየር መንገዱ ያለውን አህጉራዊ ሚና ይበልጥ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል።
የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ተግባራዊ እየተደረገ ነው
Sep 15, 2026 251
አዳማ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ) ፡- የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዝ የስንዴ ልማት እሴት ሰንሰለት ፕሮጀክት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ለኢዜአ እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የስንዴ ልማት እሴት ሰንሰለት ፕሮጀክት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። ፕሮጀክቱ የስንዴ ሰብሉ ድርቅን፣ ከፍተኛ ሙቀትን፣ ተባዮችንና ያልተጠበቀ የዝናብ መዛባትን የሚቋቋሙ የምርጥ ዘር ዝርያዎችን መጠቀም ላይ እንደሚያተኩርም ተገልጿል። በፕሮጀክቱ በስንዴ ልማቱ ላይ የሚካሄዱት የድጋፍና ክትትል ተግባራቱ በምርት ላይ ብቻ የተወሰኑ ሳይሆኑ ሙሉ የልማት የእሴት ሰንሰለቱን የሚያካትት መሆኑም እንዲሁ። ይህ አሰራር ለገበሬዎች ከዘርና ቴክኖሎጂ አቅርቦት ጀምሮ እስከ ሰብል ስብሰባ፣ ማከማቸት፣ ማቀናበርና ምርቱን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ እስከ ማቅረብ ያሉትን ሙሉ ሂደቶች ያቃልላል ተብሏል። በአጠቃላይ ሀገሪቱ የአየር ንብረት ለውጥ በሚያመጣው ተጽዕኖ ሳትበገር የስንዴ ምርቷን በማሳደግ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥና ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ለማጠናከር እያደረገች ያለችውን የተቀናጀ እንቅስቃሴ የሚደግፍ ፕሮጀክት መሆኑ ነው የተገለጸው። በግብርና ሚኒስቴር የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ አብዱልሰመድ አብዶ ለኢዜአ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ ሶማሌ እና አፋር ክልሎች ነው። በዚህም በክልሎቹ የሚገኙ 76 ወረዳዎችና 1 ሺህ 129 ቀበሌዎችን በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ለአምስት አመታት ተግባራዊ በሚደረገው በዚህ ፕሮጀክት በአካባቢዎቹ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል አነስተኛ ይዞታ ያላቸው ስንዴ አምራች አርሶ አደሮችን ገቢ ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህ ረገድ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል የዘር ግብዓት አቅርቦት ዋነኛው መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም በየደረጃው ከሚገኙ የግብርና ምርምር ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ፕሮጀክቱ ተግባራዊ በተደረገባቸው ባለፉት ሁለት አመታት ውስጥ የዳቦና የመኮሮኒ ስንዴ ዘርን በጥራት በማምረት በፕሮጀክቱ ለታቀፉ አርሶ አደሮች ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። ይህም የመነሻ ዘር አቅርቦት ከማሻሻል ባለፈ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ማስቻሉን አመላክተዋል። ፕሮጀክቱ ከአፈር ለምነትና ጤንነት ጋር ተያይዞ ስንዴ አምራች በሆኑ አካባቢዎች እያጋጠመ ያለውን ሰፊ የአሲዳማነት ችግርንም ለማቃለል ትኩረት መስጠቱን አስተባባሪው አስታውቀዋል። በዚህ ረገድ ስለ ኖራ አጠቃቀም ለአርሶ አደሩ በሰርቶ ማሳያ በማሳየት በአሲዳማነት የተጠቃ አፈርን በማከም ምርታማነት እንዲሻሻል በፕሮጀክቱ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። የኖራ አቅርቦትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ትላልቅ የኖራ ወፍጮዎች እየተተከሉ ሲሆን፣ ለአፈር ለምነት የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ ስራም ተያይዞ እየተከናወነ ነው ብለዋል። ለመስኖ ልማት አመቺ በሆኑ አካባቢዎች የ18 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ የጠቆሙት ኃላፊው፣ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሜካናይዜሽን ማዕከላትን ከመገንባት ጎን ለጎን በአራቱ ክልሎች 49 ትላልቅና መካከለኛ የስንዴ ማከማቻ መጋዘኖችን የመገንባት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል። ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ 94 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው ይህ ፕሮጀክት፣ መንግሥት የስንዴን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ለያዘው ስትራቴጂ ስኬታማነት ወሳኝ ድርሻ አለው ብለዋል።    
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጥራት ደረጃውን የጠበቀ ቡና በብዛት ለማዕከላዊ ገበያ ይቀርባል
Sep 14, 2026 340
ዲላ፣ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው በጀት አመት ቡናን በጥራት እና በብዛት አዘጋጅቶ ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ ከወዲሁ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ቡናና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ገለጸ። ክልላዊ የቡና ምርት አሰባሰብና ተጓዷኝ ተግባራት ላይ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ ተካሂዷል።   የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል ብሩ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ የቡና አመራረትና ዝግጅት እየተሻሻለ በመምጣቱ ምርታማነትና ጥራትን ማሳደግ ተችሏል። ከክልሉ በተያዘው 2019 በጀት አመት ቡናን በጥራት በማዘጋጀት በብዛት ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ በየደረጃው በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በበጀት አመቱ ከ48 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማእከላዊ ገበያ እንደሚቀርብ አመላክተዋል። ጥራት ላለው ቡና የተሻለ ዋጋ መቆረጡ የዘርፉን ተወዳዳሪነት አሳድጓል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን የቡና ላኪዎች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ኢያሱ ወራሳ ናቸው።   ባለፈው ዓመት ቡናን በጥራት ከማዘጋጀት ባለፈ በጊዜ ለገበያ እንዲቀርብ መደረጉ ተጠቃሚነታችን እንዲረጋገጥ አስችሏል ብለዋል፡፡ በተያዘው ምርት ዘመንም ጥራት ያለው ቡና ለገበያ ለማቅረብ ከወዲሁ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን አመልክተዋል። ቡና ላኪ አርሶ አደር አሰለፈች ጋን በበኩላቸው የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በመጠቀም ምርታማነትን ማሳደግ መቻላቸውን ተናግረዋል። በተያዘው ዓመትም ከማሳቸው የሚያገኙትን የቡና ምርት በጥራት በማዘጋጀት በቀጥታ የገበያ ትስስር ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በመድረኩ አምራቾች፣ ላኪ አርሶ አደሮች፣ አቅራቢ ነጋዴዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።    
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አኩቴክ ዲያግኖስቲክ የህክምና ቱሪዝም ማዕከልነት ግብ ለማሳካት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው
Sep 15, 2026 295
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ አኩቴክ ዲያግኖስቲክ ሀገሪቱን የህክምና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የአኩቴክ ዲያግኖስቲክ ዋና ዳይሬክተር ሄኖክ ታደሰ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በቅርቡ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የሥራ እንቅስቃሴ መመልከታቸው ይታወሳል።   በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ አኩቴክ (ACCU-TECH) ዲያግኖስቲክ ላቦራቶሪ የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ ወደ ከፍተኛ ምዕራፍ የሚያሸጋግር እና ለዘርፉ ልዩ መለያ እና አቅም ነው። ዘመናዊው ላቦራቶሪ በአንድ ጊዜ በርካታ ናሙናዎችን በመቀበል ለተወሰነ ጊዜ ሳምፕሎችን በጥንቃቄ ማቆየት የሚያስችል አቅም እንዳለውም ተናግረዋል። የአኩቴክ ዲያግኖስቲክ ዋና ዳይሬክተር ሄኖክ ታደሰ ለኢዜአ እንዳሉት፣ ስያሜው "አኩ" ትክክለኛነትን እና "ቴክ" ቴክኖሎጂን የሚወክል ሲሆን፣ የሚጠቀማቸው ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎች የምርመራ ውጤቶች ጥራት እንዲኖራቸው ያስችላሉ። ይህ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ ላቦራቶሪ ወደ ውጭ ሀገር ተልከው ይሠሩ የነበሩ የላቦራቶሪ ምርመራዎችን በማስቀረት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ገልጸዋል።   የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ከሪቲና ፋርማሲዩቲካል ጋር በመተባበር የተቋቋመው ላቦራቶሪ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ አውቶሜትድ የሆነ ነው ብለዋል። ላቦራቶሪው በምርመራ ሂደቶች ላይ የሚታዩ የውጤት መዘግየቶችንና የውጭ ምንዛሬ ወጪዎችን ለማስቀረት ጉልህ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም እስከ 68 በመቶ የሚደርሱ ስህተቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ አንስተው፣ አሁን ያለው ሲስተም ይህንን ዲጂታላይዝ በማድረግ ስህተቱን ወደ ዜሮ እንደሚያወርደው አስረድተዋል። ላቦራቶሪው በርካታ ናሙናዎችን በአንድ ጊዜ የመመርመር ብቃት ያለው ከመሆኑ ባሻገር ናሙናዎችን በጥንቃቄ የሚያቆይ መሆኑንም ተናግረዋል። ማሽኖቹ ከሰው ሰራሽ አስተውሎት (አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ) ጋር የተገናኙ በመሆናቸው ሥራን በቀላሉና በፍጥነት እንዲያከናውኑ ማስቻሉን አንስተዋል። በቀጣይም አገልግሎቱን በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ በድሮን ናሙና መሰብሰብ የሚያስችል ተግባር ለማከናወን እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ላብራቶሪው ሀገሪቱን የህክምና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካትም ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ተናግረዋል።
የመደመር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት እንድትመራ ትልቅ ሚና ይጫወታል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 12, 2026 394
አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ):- አፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት እንድትመራ የመደመር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ዛሬ በህንድ ኒው ዴልሂ መካሄድ ጀምሯል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ንግግር አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ዓለም አቀፍ ቀውሶች የሚያስከትሉት ጉዳት በአንድ ዘርፍ ላይ ብቻ ሳይወሰኑ ተደራራቢ መስተጓጎል እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል። ሀገራት ቀውሶች ከመከሰታቸው በፊት የመቋቋም አቅም ሊገነቡ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ ፈተናን መቋቋም የሚያስችሉ ስርዓቶችን እየገነባች እንደምትገኝ ተናግረዋል። መንግስት በምግብ ዋስትና ላይ ባከናወነው ተግባር ኢትዮጵያ ከውጭ ከሚገባ ስንዴ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ ወጥታ ራሷን መቻሏን ጠቅሰዋል። በመሆኑም ሀገሪቱ ለታቀደው የብሪክስ የሰብል ልውውጥ ማዕቀፍ (BRICS Grain Exchange) እንደ አምራችም ሆነ አቅራቢ ሆና ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል። በጤናው ዘርፍም የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ትልቅ ትምህርት መስጠቱን ነው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የሚያጋጥሙ ቀውሶችን ለመቋቋም የሀገር ውስጥ የማምረት አቅሟን እያሳደገች እንደምትገኝ ገልጸው፤ የፋርማሲዩቲካልና የመድኃኒት ማምረቻዎችንም እያስፋፋች መሆኗን ጠቁመዋል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ ዲጂታል መሠረተ ልማት፣ ዲጂታል መታወቂያ (Digital ID)፣ የክፍያ ሥርዓቶች እና የመረጃ ልውውጥ በስፋት እየተገነቡ መሆናቸውን አንስተዋል። መረጃዎች ደህንነታቸው በተጠበቀ መልኩ በሕግ አግባብ ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ይህንን ለውጥ የበለጠ እንደሚያጠናክረው አመልክተዋል። በቀጣዩ ትውልድ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ይበልጥ ሰዎችን ማገልገል፣ ብዙ ቋንቋዎችን መረዳት እና ሰፊ የሰው ልጅ እውቀት ማካተት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል። አፍሪካ የነገውን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን በባለቤትነት ለመምራት የምርምር፣ የኮምፒውቲንግ አቅም፣ ክህሎት እና ተቋማት እንደሚያስፈልጋት አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ እየገነባች ያለችውም የመደመር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲም አፍሪካ የወጠነችውን ግብ የማሳካት አላማ እንዳለው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ አፍሪካን የሚወክል የቴክኖሎጂ አቅም ለመገንባት ከብሪክስ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላትም ገልጸዋል። በተጨማሪም ሰዎችን ማዕከል ያደረገ የኤአይ አስተዳደር መደገፍ እንዳለበት እና ጥሩ አስተዳደር ከብቃት ጋር ሊጣጣም እንደሚገባ አሳስበዋል።
የሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር የዲጂታል ግብር ክፍያ ሥርዓት ጀመረ
Sep 12, 2026 253
ሰመራ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ)፦የአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር የዲጂታል ግብር ክፍያ ሥርዓት ጀመረ። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሰመራ ሎጊያ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር አህመድ ኑርሳሊም፤ የዲጂታል የግብር ክፍያ ሥርዓት ቀልጣፋ አሰራርን ከመዘርጋት ባለፈ ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሚያስችል ዘመናዊ አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።   የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ለብልሹ አሰራር እንዳይጋለጥ እና የግብር መሰወር ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ግብር ከፋዮች ምንም አይነት እንግልት ሳይገጥማቸው ባሉበት ሆነው የሚከፍሉበት ስርአት መዘርጋቱ አስደሳች መሆኑን ተናግረዋል። ግብር ከፋዮች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና በቴሌብር አማራጮች ባሉበት ሆነው ግብራቸውን በመክፈል ከእንግልት በጸዳ መልኩ ሃላፊነታቸውን በቀላሉ መወጣት ያስችላቸዋል ብለዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኀላፊ ኡመር ኑር እና ሌሎችም የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ስፖርት
አርሰናል እና ሊቨርፑል በካራባኦ ካፕ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ
Sep 16, 2026 154
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ የሶስተኛ ዙር ጨዋታዎች ማምሻውን ተካሄደዋል። በፖርትማን ሮድ በተደረገው ጨዋታ አርሰናል ኤፕስዊች ታውንን 4 ለ 2 ረትቷል። የ16 ዓመቱ ታዳጊ ማክስ ዶውማን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኖኒ ማዱዌኬ እና ሚኬል ሜሪኖ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። አኒስ ሜህመቲ እና ቹባ አክፖም የኤፕስዊችን ግቦች አስቆጥረዋል። በሌላኛው መርሐ ግብር ሊቨርፑል ቶተንሃም ሆትስፐርስን 3 ለ 1 አሸንፏል። በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አሌክሲስ ማካሊስተር፣ ኮዲ ጋፕኮ እና ዶምኒክ ስቦዝላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ኮኖር ጋላገር የቶተንሃምን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ብሬንትፎርድ ሬዲንግን 2 ለ 1፤ ፉልሃም ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 2 አሸንፈዋል። ፒተርቦሮው ባርንስሌይን በመለያ ምት ረትቷል። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል፣ ሊቨርፑል፣ ብሬንትፎርድ፣ ፉልሃም እና ፒተርቦሮው ወደ አራተኛ ዙር አልፈዋል።
የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ ሊካሄድ ነው
Sep 15, 2026 127
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):- 22ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እ.አ.አ በ2029 በኬንያ ናይሮቢ ይደረጋል። የዓለም አትሌቲክስ ምክር ቤት በሀንጋሪ ቡዳፔስት ባካሄደው ስብስባ የ2029 እና የ2031 ውድድር አስተናጋጅ ከተሞችን ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሰረት እ.አ.አ በ2029 22ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በኬንያ እንዲካሄድ ምክር ቤቱ ወስኗል። የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአፍሪካ ምድር ሲካሄድ በውድድሩ የ43 ዓመታት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ናይሮቢ የ2029ን ውድድር ማስተናገዷ ለአፍሪካ አትሌቲክስ ታሪካዊ ምዕራፍ የሚከፍት ነው። ኬንያ ከዚህ ቀደም የዓለም ከ18 ዓመት በታች እና ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮናዎችን እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆነውን «ኪፕ ኬይኖ ክላሲክ» ውድድር ማስተናገዷ ለዚህ ስኬት ትልቅ መሠረት ሆኗታል። የጀርመኗ ከተማ ሙኒክ እ.አ.አ በ2031 የሚካሄደው 23ኛውን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እንድታስናግድ ተመርጣለች። ሙኒክ ሻምፒዮናውን ስታስተናግድ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ መሆኑን የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ ውሳኔውን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት፣ አስተናጋጅ ከተሞችን ለመምረጥ የተደረገው ሂደት አጓጊ እንደነበር ገልጸዋል። ናይሮቢ እና ሙኒክ ለአህጉራቱ ልዩ ዕድሎችን የሚያመጡ አሳማኝ እቅዶችን በማቅረባቸው ሊመረጡ መቻላቸውን ተናግረዋል። 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እ.አ.አ በ2027 በቻይና ቤጂንግ ይካሄዳል። የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እ.አ.አ በ1983 በፊንላንድ ሄልሲንኪ የተጀመረ ውድድር ነው።
ኢትዮጵያ የምትሳተፍበት ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዛሬ ይጀመራል
Sep 15, 2026 129
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):- በታንዛንያ አዘጋጅነት የሚካሄደው ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ዛሬ ጅማሮውን ያገኛል። በውድድሩ ላይ ዘጠኝ ሀገራት በሶስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በምድብ አንድ ከአዘጋጇ ታንዛንያ እና ሩዋንዳ ጋር ተደልድሏል። በአሜሪካዊው ቤንጃሚን ዚመር የሚመራው ብሔራዊ ቡድን መስከረም 7 ከሩዋንዳ እና መስከረም 9 ከአዘጋጇ ታንዛንያ ጋር ይጫወታል። በምድብ ሁለት ዩጋንዳ፣ ሱዳን እና ጅቡቲ እንዲሁም በምድብ ሶስት ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያ እና ብሩንዲ ይገኛሉ። ዛሬ በውድድሩ መክፈቻ ቀን በምድብ አንድ አዘጋጇ ታንዛንያ ከሩዋንዳ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። በምድብ ሁለት ዩጋንዳ ከጅቡቲ ከቀኑ ስምንት ሰዓት፣ በምድብ ሶስት ደቡብ ሱዳን ከብሩንዲ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ቡድኑ ወደ ግማሽ ፍጻሜ የሚገባው ከምድቡ አንደኛ ወይም ከሶስቱ አጠቃላይ ምድቦች ምርጥ ሁለተኛ ሆኖ ካጠናቀቀ ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በጋና እ.አ.አ በ2027 ለሚካሄደው ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በማጣሪያ ውድድሩ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆን ይኖርበታል። ብሔራዊ ቡድኑ በጋና በሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ብሔራዊ ቡድኑ ካለፈ እና ግማሽ ፍጻሜ መድረስ ከቻለ በዛው ዓመት በአዘርባጃን እና ኡዝቤኪስታን ጣምራ አዘጋጅነት ለሚካሄደው ከ20 ዓመት በታች የፊፋ ዓለም ዋንጫ ማለፉን ያረጋግጣል። የሴካፋ ዞን ማጣሪያ እስከ መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ ዘላቂና የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አረንጓዴ ኢኮኖሚ የመገንባት ራዕይዋን ውጤታማ በሆነ መልኩ አጠናክራ ቀጥላለች
Sep 15, 2026 189
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ዘላቂና የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አረንጓዴ ኢኮኖሚ የመገንባት ራዕይዋን ውጤታማ በሆነ መልኩ አጠናክራ መቀጠሏን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው የኖርዲክ-አፍሪካ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ (Nordic Africa EV Summit) ጉባኤ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው።   ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት አረንጓዴና የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የልማት ስትራቴጂን በሀገራዊ የልማት ዕቅዷ ማዕከል አድርጋ እየሰራች ትገኛለች። የአረንጓዴ አሻራ፣ የታዳሽ ኃይል ማስፋፋት፣ የአረንጓዴ ከተማ ልማት እና ዝቅተኛ የካርቦን ልቀት ያለው ኢኮኖሚ የመገንባት ጥረት ኢትዮጵያ የልማት አቅጣጫዋን ለመለወጥ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። የሀገሪቱ የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት ስትራቴጂ የትራንስፖርት ዘርፉን ከካርቦን ነፃ ማድረግን ዋነኛ መንገድ አድርጎ ማስቀመጡንም ጠቁመዋል።   የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የሕዝብ ትራንስፖርትን፣ የአረንጓዴ ከተማ ኮሪደሮችን እና ንፁህ የትራንስፖርት ሥርዓቶችን ከታዳሽ ኃይል አቅም ጋር የማዋሃድ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል። ይህ ጥረት ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን፣ የኃይል ደህንነት፣ የቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ የኢንዱስትሪ ልማት እና የዜጎችን የኑሮ ጥራት የማሻሻል አጀንዳ መሆኑን አስገንዝበዋል።   የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ግንኙነት እና መሠረተ ልማት ክፍል ዳይሬክተር ሮበርት ታማ ሊሲንጌ በበኩላቸው፤ በአፍሪካ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የመጠቀምና የማምረት አጠቃላይ አዝማሚያ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። አህጉሪቱ ኃይል በማመንጨት ላይ ብቻ ሳትወሰን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲሁም ወደ አውሮፓና እስያ ለመላክም መስራት እንዳለባት ገልጸው፤ ሀገራት ተሽከርካሪዎቹን ለማስገባት የሚያስችሉ ማበረታቻዎችንና የተሟላ ስነ-ምህዳር በመፍጠር ላይ እንደሚገኙ አብራርተዋል።   የኖርዲክ-አፍሪካ ኢቪ ሳሚት ሮድ ቱ አፍሪካ የሀሳብ መሪ ሚከል ቤከር አከርቪክ እንደተናገሩት፤ ከተሞችን ከካርቦን ነፃና ንፁህ አየር እንዲኖር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። በትራንስፖርት ዘርፍ የሚፈጠረው የልቀት መጠን ከፍተኛ በመሆኑ፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን አሰራር መተግበር በኢኮኖሚ ደረጃ ብቻ ሳይሆን ለአካባቢ ጥበቃም እውነተኛ ትራንስፎርሜሽን እንደሚያመጣ አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም፣ አረንጓዴ እና ዘላቂ የትራንስፖርት ስርዓትን ለመገንባት በቁርጠኝነት እየሰራች ነው
Sep 15, 2026 194
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም፣ አረንጓዴ እና ዘላቂ የትራንስፖርት ስርዓትን ለመገንባት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለፁ። ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው የኖርዲክ-አፍሪካ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ (Nordic Africa EV Summit) ጉባኤ ላይ ነው።   ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት አረንጓዴና የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የልማት ስትራቴጂን በሀገራዊ የልማት ዕቅዷ ማዕከል አድርጋ እየሰራች ትገኛለች። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የታዳሽ ኃይል ማስፋፋትና ዝቅተኛ ካርቦን ያለው ኢኮኖሚ የመገንባት ጥረት የዚሁ ቁርጠኝነት ማሳያ መሆናቸውን አብራርተዋል። የትራንስፖርት ዘርፉን ከካርቦን ነፃ ማድረግ ለዘላቂ ኢኮኖሚ ግንባታ ከሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አንዱ መሆኑን አመልክተው፤ ሀገሪቱ ይህንን ውሳኔ ወደ ተግባር ለመቀየር የኤሌክትሪክ ህዝብ ትራንስፖርት፣ የአረንጓዴ ከተሞች ኮሪደር እና የፅዱ አየር ትራንስፖርት ስርዓትን ከታዳሽ ኃይል አቅሟ ጋር አስተስስራ እየገነባች እንደሆነ ገልፀዋል። የኤሌክትሪክ ትራንስፖርት ሽግግር ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን፣ ለኃይል ዋስትና፣ ለቴክኖሎጂ ፈጠራና ለዜጎች የህይወት ጥራት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል። ተሽከርካሪዎችን ብቻ ወደ ሀገር ማስገባት የኤሌክትሪክ ትራንስፖርት ምህዳርን ሙሉ በሙሉ ሊፈጥር እንደማይችል አመልክተው፤ የተሟላ ውጤት ለማስመዝገብ መሰረተ ልማቶችና አሰራሮች ማሟላት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በዚህም የቻርጅ ማድረጊያ መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋትና የዲጂታል አሰራርን መዘርጋት፣ ሁለንተናዊ ስታንዳርዶችን ማዘጋጀት፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት (ኢንጂነሮችንና ቴክኒሻኖችን ማሰልጠን) እንዲሁም የባትሪዎችን መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡   በመሆኑም የተቀናጀ ስርዓት መገንባት፣ ከቴክኖሎጂ ገዢነት ወደ ሀገር ውስጥ አቅም ግንባታ መሸጋገር እንዲሁም ቀጣናዊና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያና አፍሪካ ከኖርዲክ ሀገራት አዎንታዊ ተሞክሮዎችን እንደሚወስዱ የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ ሆኖም የአፍሪካ መፍትሔዎች የአህጉሪቱን እውነታና የትራንስፖርት ፍላጎት ያገናዘቡ መሆን እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል። አፍሪካ ወደ ኤሌክትሪክ ሞቢሊቲ የምታደርገው ሽግግር የኢንዱስትሪ ልማት ሞተር እንጂ ለውጭ ምርቶች ሌላ ገበያ መዳረሻ ብቻ መሆን እንደሌለበት አስገንዝበዋል፡፡ አፍሪካውያን በጠቅላላው የእሴት ሰንሰለት ውስጥ እንዲሳተፉ የሀገር ውስጥ ገጣጣሚዎችንና አምራቾችን ማጠናከር፣ በምርምርና ልማት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንዲሁም ድንበር ተሻጋሪ የትራንስፖርት ስርዓቶችን ማስተሳሰር እንደሚገባ ገልፀዋል። ለዚህ ትራንስፎርሜሽን የመንግስት ሀብት ብቻውን በቂ አለመሆኑን ጠቁመው፤ በመንግስታት፣ በልማት አጋሮች፣ በንግድ ባንኮችና በግል ባለሀብቶች መካከል ጠንካራ አጋርነት መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። ጉባኤው ከውይይት ባለፈ ወደ ተግባራዊ እርምጃዎች የሚወሰዱበት፣ ግልጽ ግቦች የሚቀመጡበት እንዲሁም የልማትና ቴክኖሎጂ አጋሮች ትብብር የሚጠናከርበት መድረክ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር አፍሪካ ለችግሮቿ መፍትሔ ማቅረብ እንደምትችል ማረጋገጫ ነው
Sep 13, 2026 446
አዲስ አበባ፤መስከረም 3 /2019 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር አፍሪካ ለችግሮቿ መፍትሔ ማቅረብ እንደምትችል ማረጋገጫ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም፣ ሥነ-ምህዳርን በመመለስና ዘላቂ ልማትን በማረጋገጥ ለአፍሪካና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አርዓያ የሚሆን ተግባር እያከናወነች መሆኑንም ተናግረዋል። በተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚክ ኮሚሽን የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ባለሙያ ዮሴፍ አምሃ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከከባቢ አየር የሚለቀቁ ሙቀት አማቂ ጋዞችን በመያዝ ለሥነ-ምህዳር ጥበቃ ገንቢ ሚና እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል። መርሃ ግብሩ ለአርሶ አደሩ፣ ለወጣቶችና ለሴቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል። የፓን አፍሪካ አየር ንብረት ፍትህ ጥምረት ዋና ዳይሬክተር ሚቲካ ምወንዳ (ዶ/ር)፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ሀገራት ችግራቸውን በራሳቸው አቅም ለመፍታት ሊወስዱት የሚገባ ምርጥ ተሞክሮ መሆኑን ገልጸዋል።   ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ያስመዘገበችው ስኬት አፍሪካ ለችግሮቿ መፍትሔ ማቅረብ እንደምትችል ያሳየ ነው ብለዋል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ የአየር ንብረት ሻምፒዮንና የአፍሪካ የግሬት ግሪን ዋል ኢኒሼቲቭ አምባሳደር ታቢ ጆዳ፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በጠንካራ አመራር የታጀበ ውጤታማ ሥራ መሆኑን ገልጸዋል።   መንግሥት ፕሮግራሙን ከንግግር ባለፈ መሬት ላይ የሚታይና ሚተረጎም ድንቅ ኢኒሼቲቭ ነው ብለዋል። በአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ አየር ንብረትና ልማት ልዩ ፈንድ አስተዳዳሪ ጀምስ ኪንያንጊ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ እርምጃዎችን በመቅረጽና በተግባር ረገድ ለአፍሪካውያን አርዓያ መሆኗን ገልጸዋል።  
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ስኬታማ ሥራ ተከናውኗል
Sep 10, 2026 349
የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር በ2011 ዓም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በይፋ መጀመሩ ይታወቃል። መርሃ ግብሩ እንደ ሀገር ያጋጠሙ በርካታ የዘላቂ ልማት ተግዳሮቶችን የመሬት መጎሳቆል የደንና ብዝሃ ህይወት መጨፍጨፍ፣ የውሃ አካላትን መድረቅና በደለል መሞላት ለመከላከል ታስቦ ወደ ሥራ መገባቱ ይታወቃል። በዚህም በመጀመሪያው ምዕራፍ 50 ቢሊዮን ችግኝ በማህበረሰብ ተሳትፎ ለመትከል ታቅዶ ነበር።   ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት የመርሃ ግበሩ የትግበራ ዓመታት 56 ነጥብ 8 ቢሊዮን ችግኞችን፤ በዚህ ዓመት ብቻ ደግሞ 8 ነጥብ 2 ቢሊዮን ችግኝን በመትከል በዓለም ላይ አዲስ ታሪክ ፅፋለች። አጠቃላይ ከተተከሉ ችግኞች ከ3 ቢሊዮን በላይ የሚሆኑት በአንድ ጀምበር የተተከሉ መሆናቸው በዓለም ላይ ትልቅ የችግኝ ተከላ ሆኖ ተመዝግቧል። ከተተከሉ ችግኞች 60 በመቶ የሚሆኑት የጥምር ደን ግብርና (የፍራፍሬ፣ የቡና፣ የመኖ ዝርያዎች) ሲሆኑ 35 በመቶ የደን ዝርያ ናቸው። ይህ ታላቅ የልማት ድል የተሳካው ከላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እስከ ታችኛው የመንግስት አደረጃጀት ለመርሃ ግብሩ በተሰጠው ቁርጠኛ አመራር ነው። በየዓመቱ ከ25 ሚሊየን በላይ ዜጎች በችግኝ ተከላ ተሳትፈዋል።   እስካሁን በተሠራው ሥራ በየዓመቱ ይፈጸም የነበረው የደን ጭፍጨፋ ከ92 ሺህ ወደ 27 ሺህ ሄክታር እንዲቀንስ አስችሏል። በእርሻ ማሳ የአፈር መከላት በዓመት በሄክታር ከ130 ቶን ወደ 54 ቶን ቀንሷል። አረንጓዴ ዐሻራ በየዓመቱ ወደ ውሃ አካላት የሚገባ የአፈር ደለል ከ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ቶን ወደ 208 ሚሊዮን ቶን ዝቅ እንዲል አስችሏል። በመርሃ ግብሩ ለ2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ወጣቶችና ሴቶች አረንጓዴ ሥራ ተፈጥሮላቸዋል።   በበርካታ አካባቢዎች የፍራፍሬና የደን ክላስተር እየተፈጠረ አርሶ አደሮች የላቀ የኢኮኖሚ አቅም እንዲገነቡ እያስቻለ ነው። ኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት መርሃ ግብር ቀርጻ መተግበር እንደምትችል ትልቅ ተሞክሮ የተወሰደበትና ለዓለም ያሳየችበትም ነው። ከዚህም ባለፈ ሀገራችን ዓለም እየተፈተነችበት ላለው የአየር ንብረት ለውጥ ተግባራዊ መፍትሔ በመስጠት ምሳሌ መሆኗን ያሳየችበት ነው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በቀጣናው ያሉ ፈተናዎችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራት የጋራ ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው - ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Sep 15, 2026 345
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ)፦ በቀጣናው እያጋጠሙ የሚገኙ ፈተናዎች በዘላቂነት እንዲፈቱ የአባል ሀገራት አብሮነትና የጋራ ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢጋድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት 74ኛው አስቸኳይ ስብሰባውን ዛሬ በጅቡቲ አካሂዷል። በስብሰባው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች ተሳትፈዋል። በቀጣናው ሰላም እና ጸጥታ እንዲሁም በሌሎች አበይት ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጓል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በቀጣናው እያጋጠሙ ያሉ ፈተናዎችን በዘላቂነት ለመቋቋም የአባል ሀገራት አብሮነትና የጋራ ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው።   በኢጋድ ሴክሬታሪያት በኩል የተከናወኑ የልማትና የሰላም ሥራዎች አበረታች ውጤቶችን እያስገኙ መሆናቸውን በመግለጽ፣ ተቋሙ ለቀጣናው ህዝቦች ብልጽግና መረጋገጥ የጸና አቋም እንዳለው አመልክተዋል። ምንም እንኳን የተለያዩ ጂኦፖለቲካዊ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ የኢጋድ ሴክሬታሪያት ያለፉት ስድስት ወራት አፈጻጸም አበረታች የሚባል መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣናዊ መሠረተ ልማት እና የጤና ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ያነሱት ዋና ፀሐፊው፤ የቀጣናው የከርሰ ምድር ውሃ መረጃ ሥርዓት የአገልግሎት ተደራሽነት የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ጠቁመዋል። እንዲሁም የቀጣናው ዓለም አቀፍ የጤና ሽፋን መረጃ ጠቋሚ (ኢንዴክስ) ከ60 ወደ 65 በመቶ ከፍ ማለቱንና ይህም እ.አ.አ በ2027 70 በመቶ ለማድረስ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን ነው ያነሱት። በሌላ በኩል ሱዳን ወደ ኢጋድ ሙሉ አባልነቷ መመለሷ የቀጣናውን ትብብርና አንድነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው እ.አ.አ ጁላይ 2026 ወደ ሱዳን ባቀኑበት ወቅት የኢጋድ የሱዳን ልዑክ ቢሮ በድጋሚ በይፋ መከፈቱን አስታውሰው ይህ እርምጃ ከቀጣናው ሕዝቦች ጋር ያለውን ቀጥተኛና ዘላቂ ትስስር አጠናክሮ የሚያስቀጥል መሆኑን አመላክተዋል። ኢጋድ ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኤጀንሲዎች እና ከሌሎች ስትራቴጂካዊ አጋሮች ጋር ያለው ግንኙነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ወሳኝ ነው ብለዋል። አጋርነቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን አቅም በማጠናከር ረገድ የጎላ ድርሻ እንደሚያበረክትም ነው ያነሱት። በቀጣይ ሊከሰቱ የሚችሉ የአየር ንብረት ለውጥ አደጋዎችን የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን በማጠናከር ለመቋቋም የሚያስችሉ አሰራሮች እየተቀረፁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሀገራት የኤልኒኖ (El Niño) የአየር ንብረት መዛባት የሚያስከትለውን ስጋት ለመቀነስ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንዳለባቸው አሳስበዋል። በሌላ በኩል ቀጣናውን ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር ለማስተሳሰርና በቴክኖሎጂ የታገዘ የልማት መሠረት ለመጣል የተጀመሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ገልጸዋል። ስብሰባው የቀጣናውን ሰላም፣ ደህንነት እና ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን በሚያስችሉ ሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከርና ውሳኔዎችን በማሳለፍ መጠናቀቁን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የኢጋድ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ከተቋሙ ቁልፍ የፖሊሲ አደረጃጀቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ የድርጅቱን ሥራዎች በመምራትና በአባል ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና የሚጫወት ነው።
አፍሪካ በዓለም ፊት ቦታ ለማግኘት አትማጸንም ፤ ይልቁንም የሚገባትን ስፍራ በባለቤትነት እየያዘች ነው
Sep 9, 2026 434
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ):- አፍሪካ በዓለም ፊት ቦታ ለማግኘት አትማጸንም ፤ የሚገባትን ስፍራ እና ክብር በራሷ እያረጋገጠች ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ቀን ዛሬ እየተከበረ ይገኛል። የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ቀኑን በማስመልከት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት ቀን እ.አ.አ በ1999 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለመተካት ይፋዊ ውሳኔ የተላለፈበት የሰርጥ ድንጋጌ (Sirte Declaration) የሚታወስበት እንደሆነ ገልጸዋል። በዚያን ወቅት የአፍሪካ መሪዎች አህጉራዊ ትስስርን ለማፋጠን እና የአፍሪካን ድምጽ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ለማድረግ የአፍሪካ ህብረትን ለመመስረት ወሳኝ እና ታሪካዊ እርምጃ የወሰዱበት ምዕራፍ ነው ብለዋል። የዘንድሮው የአፍሪካ ህብረት ቀን ለአህጉሪቱ እጅግ ልዩ ትርጉም ባለው ወቅት ላይ እየተከበረ እንደሚገኝ አውስተዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ የአፍሪካን እውነተኛ ቁመና እና ትክክለኛ መጠን የሚያሳይ የዓለም ካርታ አጠቃቀምን የሚደግፍ፣ በአፍሪካ መሪነት የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ አፅድቋል። በቶጎ ሃሳብ አመንጪነትና በአፍሪካ ህብረት ድጋፍ እውን የሆነው ይህ እርምጃ ከቀላል የካርታ ማስተካከያ በላይ ትርጉም አለው ብለዋል ሊቀ መንበሩ። አፍሪካ በዓለም ፊት እንዴት እንደምትታይ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን እና አፍሪካ ራሷን የምትገመግምበትንና የምታሳይበትን ትርክት ራሷ መቅረጽ እንዳለባት አበክሮ የሚያስታውስ ነው። ይህ ውሳኔ አፍሪካ በዓለም ፊት በምን መልኩ መታየት እንዳለባት ከማሳየቱም በላይ፤ አፍሪካ ራሷን የምትመዝንበትንና እውነታዋን ለዓለም የምታሳይበትን ትርክት በራሷ መቅረጽ እንዳለባት በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን ነው ያነሱት። የአፍሪካ እጣ ፈንታ የሚወሰነው በአፍሪካውያን የራሳቸው እይታ ነው። አፍሪካን በእውነተኛ ቁመናዋ፣ኃይሏ እና አቅሟ የምንመለከትበት ጊዜ አሁን ነው ብለዋል። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር አያይዘውም ካርታውን የማስተካከል እርምጃ አፍሪካ ወደ ላቀ የጋራ ራዕይ የምታደርገው አህጉራዊ ጉዞ አካል መሆኑን አንስተዋል። ይህም በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠና (AfCFTA) አማካኝነት የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከርን፣ ሰላም እና ፀጥታን ማረጋገጥን፣ ዘላቂ ልማትን እውን ማድረግን እና በዓለም አቀፍ ውሳኔ ሰጪ አካላት ውስጥ የአፍሪካን ተሳትፎ ማሳደግን እንደሚያካትት በዝርዝር አስረድተዋል። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የተሳሰረች፣ የበለጸገች እና ሰላማዊት አፍሪካን ለመገንባት የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ሰላም እና ፀጥታን ማረጋገጥ፣ የኢኮኖሚ ትስስርን በማፋጠን እና የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ተሰሚነት መጨመር የአፍሪካ ህብረት ቀዳሚ ትኩረቶች ናቸው ብለዋል። አፍሪካ በዓለም ፊት እውቅና ለማግኘት አትለምንም፤ ይልቁንስ በዓለም አቀፍ መድረክ የሷ የሆነውን ትክክለኛ ስፍራ በራሷ ባለቤትነት እየያዘች ነው። አሁን የሚጠበቅብን ይህንን ጠንካራ እምነት ወደ ህብረት፣ ሀብትና ብልጽግና፣ ሰላም እና ተደማጭነት መለወጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ሊቀመንበሩ አፍሪካ የምታስመዘግበው እድገት በዓለም አቀፍ መድረኮች በሚኖራት ውክልና ብቻ ሳይሆን፣ በዜጎቿ ላይ የኑሮ ጥራት መሻሻል ጭምር መለካት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል። በዚህም መሰረት የአፍሪካ ህብረት የ2026 ዓመት ትኩረቱን በዘላቂ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አገልግሎት ላይ ማድረጉ፣ ህብረቱ አህጉራዊ ራዕዮችን ከዕለት ተዕለት የዜጎች ህይወት ጋር ለማያያዝ ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አመልክተዋል። በአፍሪካ ህብረት ቀን አከባበር አባል ሀገራት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የአፍሪካ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ሴቶች እና ወጣቶች ተባብረው ይበልጥ የተሳሰረች፣ በራሷ አቅም የምትተማመን እና የራሷን እጣ ፈንታ በራሷ መወሰን የምትችል አፍሪካን እንዲገነቡ ሊቀመንበሩ ጥሪ አቅርበዋል። የምንፈልጋት አፍሪካ የሚለውን አህጉራዊ ራዕይ እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ እና የሰርት ድንጋጌ ለቀጣዩ የአፍሪካ ትውልድ ዘላቂ የትምህርት እና የዕድገት መሰረት ሆኖ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የነገዋ አፍሪካ በካርታ ላይ ብቻ የተሻለ ውክልና ያላት ብቻ ሳትሆን፤ በዓለም አቀፍ መድረክ ሉዓላዊነቷ የጸና፣ ጠንካራ ውስጣዊ አንድነት ያላት፣ ለህዝቦቿም ዘላቂ ብልጽግናን የምታጎናጽፍ አህጉር መሆን ይኖርባታል ነው ያሉት። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር ለመላው አፍሪካውያን እና በውጭ ሀገር ለሚገኙ የአፍሪካ ዳያስፖራዎች ሰላማዊ እና የትብብር መንፈስ የተሞላበት የአፍሪካ ህብረት ቀን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ አጋርነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Sep 4, 2026 621
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 29/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን እና ሁሉን አቀፍ ትብብራቸውን የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ውይይቱ በአፍሪካ ህብረትና አሜሪካ መካከል ያለውን ለረጅም ጊዜ የቆየ አጋርነት ማጠናከር እና በአህጉሪቱ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር የአፍሪካና አሜሪካን ትብብር ታሪካዊ መሆኑን አውስተው በህብረቱ፣ በአባል ሀገራት እና በአሜሪካ መካከል የሁለቱንም ወገኖች ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ ጠንካራ አጋርነት መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል። በምስራቅ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሱዳን እየተደረጉ ላሉ አፍሪካ መር የሰላም ጥረቶች አሜሪካ እያደረገች ላለው ገንቢ አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያ በበኩላቸው አፍሪካ አሜሪካ ቀዳሚ ትኩረት የምትሰጣት አህጉር እንደሆነች ገልጸዋል። የጋራ ፍላጎቶችንና ግቦችን ከህብረቱ ኮሚሽንና ከአባል ሀገራት ጋር በመሆን ለማሳካት ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በዲፕሎማሲ፣ እንዲሁም በሰላምና ጸጥታ ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባም አመልክተዋል። በውይይቱ ላይ በሱዳን ጉዳይ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የሰብአዊ እርዳታ ያለ ገደብ እንዲገባ እና በሲቪሎች የሚመራ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመር አጽንዖት ተሰጥቷል። በአፍሪካ ባለቤትነት የሚመሩ የሰላም ጥረቶች እና አሜሪካ የምትደግፋቸው የሰላም ሂደቶች በተቀናጀ መልኩ ለመተግበር ከስምምነት ላይ ተደርሷል። በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመሰረተ ልማት እና በሰላም መስኮች የሁለቱን ወገኖች ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ የትብብር መስኮች ተገምግመዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ህብረትና በአሜሪካ ስትራቴጂክ ኢንቨስትመንት ማዕቀፍ ውስጥ የተደረጉ ስምምነቶችን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። በሊቢያ ጉዳይ ዘላቂ የፖለቲካ መፍትሄ ማግኘት እንደሚያስፈልግም ተነስቷል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር እና ረዳት ሚኒስትሩ የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና የትብብር አድማሱን ለማስፋት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 1925
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ሐተታዎች
ጤናማ ዜጋ አምራች ሀገር፤ የመደመር መንግሥት የጤና ፖሊሲ ትሩፋት
Sep 15, 2026 194
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ ነገን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የተገበረችው አዲስ የጤና ፖሊሲ የመደመር መንግስት ቃልን በተግባር የመተርጎም ብቃትን ከሚያመላክቱ ትሩፋቶች መካከል ተጠቃሽ ነው። የመደመር መንግስት ባለፉት ስምንት ዓመታት ትኩረት ከሰጠባቸው ዘርፎች መካከል ማህበራዊ ልማት ዘርፉ ተጠቃሽ ነው። በዚሀ ዘርፍ ከሚመደቡት መካከል ደግሞ የጤና ዘርፉ ተጠቃሽ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ፍትሃዊ እና ተደራሽ የጤና አገልግሎት ማግኘት የሚችልበትን ዕድል ለመፍጠር የፖሊሲ ማሻሻያ ማድረግን ጨምሮ የጤና መሰረተ ልማት ግንባታ እና የሰለጠነ የጤና ባለሙያ አቅም ግንባታ ላይ ውጤታማ ተግባራት አከናውኗል። ቅድሚያ መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገውን የጤና ፖሊሲ በመከለስ ለአክሞ ማዳንም ትኩረት እንዲሰጥ መደረጉን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግስት ባለፉት ዓመታት በዘርፉ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በርካታ ሆስፒታሎች ተገንብተው ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረጉንና በዚህም በዘርፉ ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።   የመደመር መንግስት የህብረተሰቡ ጤና በተሟላ መልኩ ሲጠበቅ ምርታማነት ላይ ሊያመጣ የሚችለውን አዎንታዊ ሚና በሚገባ በመረዳት ከጤና መሰረተ ልማት ባሻገር ህብረተሰቡ አስቀድሞ ጤናውን ለሚጠብቅባቸው መሰረተ ልማቶች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ለዚህ ነው በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያሉ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ልማት ላይ በትኩረት እየሰራ የሚገኘው ይህ የመንግስት ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ የግል ዘርፉም የህብረተሰቡን ጤና ከመጠበቅ እና ለፖሊሲው ውጤታማነት በኩሉን ድርሻ መወጣት የሚችልበት ዕድል ተፈጥሯል። ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የተገበረችው አዲስ የጤና ፖሊሲ እና በዘርፉ የወሰደቻቸው ውጤታማ እርምጃዎች አይበገሬ የጤና ስርዓት መዘርጋት አስችሏታል። መንግስት ጤናው የተጠበቀ ማህበረሰብ ለሀገር እድገትና ብልፅግና ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ ባለፉት ዓመታት ውጤታማ የፖሊሲ ማሻሻያ እርምጃዎች በመውሰዱ የጤና ቱሪዝም ተወዳዳሪነትን የሚያሳድጉ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ከለውጡ በፊት ኢትዮጵያ ስትከተል የቆየችው በሽታ መከላከል ላይ ብቻ ያተኮረው የጤና ፖሊሲ፣ በጤና አገልግሎት አሰጣጥና የተቋማት ግንባታ እንዲሁም በዘርፉ ቴክኖሎጂ ከመጠቀም አንጻር ክፍተት ይታይበት ስለነበር ውጤታማነቱ ላይ የራሱን ተግዳሮት ደቅኖ ቆይቷል። የመደመር መንግስት የጤናው ዘርፍ ፖሊሲ ምሉዕ የሚሆነው በሽታ መከላከል ላይ ብቻ በማተኮር ሳይሆን አክሞ ማዳንንም የፖሊሲው የትኩረት ማዕከል ማድረግ ሲቻል መሆኑን በማመነ ፖሊሲው ይህንን ባካተተ መልኩ እንዲሻሻል አድርጓል። በተጨማሪም አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ማድረግ የሚያስችሉ ለጤና መሰረተ ልማት ግንባታ ለአካታች የጤና አገልግሎት ለጤና ፋይናንስ እና ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም ውጤታማነት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በመንግስትም ሆነ በግል ዘርፉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ያካተቱ በርካታ የጤና መሰረተ ልማቶች ተገንብተው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ ተደርጓል።   ለዚህም ይመስላል በአዲስ አበባ ከተማ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን በማዘመን፣ በማስፋፋትና ጥራቱን በማሳደግ ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ መሳሪያዎችን በማስገባት የጤናውን ዘርፍ ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ መናገራቸው። በጤው ዘርፍ የአገልግሎትን ጥራት፣ ተደራሽነትና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ቁለፍ ጉዳይ ነው። የመደመር መንግስት እነዚህን ችግሮች ለማቃለል ለአዳዲስ ሆስፒታሎች እና ጤና ጣቢያዎች ግንባታ እንዲሁም ለነባሮቹ የጤና ተቋማት የማሻሻያ እና የማዘመን ተግባራት በመከናወናቸው በአገልግሎት ጥራት ተደራሽነትና ፍትሃዊነትን ከማረጋገጥ አንጻር ውጤቶች ተመዝግበዋል። በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የህክምና ተቋማትን በዘመናዊ የህክምና ግብዓት ማደራጀትና አቅማቸውን ማሳደግ ፍትሃዊ እና ተደራሽ የሆነ እንዲሁም አስተማማኝ የህክምና አገልግሎት በመስጠት የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተያዘውን ርዕይ ለማሳካት አይነተኛ ሚና ይኖረዋል። ባለፉት ስምንት ዓመታት በጤና ዘርፍ የነበሩ ክፍተቶችን መቅረፍ የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን የሚገልጹት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚህም የመንግስት የጤና ተቋማት ቁጥርና የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ማደጉን በመጥቀስ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድን ሽፋን እና የዜጎች ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ለዘርፉ ዕድገት ጥሩ ማሳያ ነው።   ባለፉት ስምንት ዓመታት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት እምርታ መመዝገቡን የመድሃኒት፣ የክትባት እና የህክምና ግብዓቶች ምርት አቅርቦት እና ቁጥጥር መጨመሩን እንዲሁም በጤና ፋይናንስ ስርዓት ላይ የተመዘገበውን ለውጥ በማሳያነት ይጠቅሳሉ። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በተለይ በጤናው ዘርፍ የተከሰቱ ዓለም አቀፍ ወረርሽኞችንና በዘርፉ የተስተዋሉ ተግዳሮቶችን ወደ ዕድል በመቀየር አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ ችላለች። በዚህም የወረርሽኝ ልየታ እና ቁጥጥር፣ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ የጤና ባለሙያዎችን ማብቃትና ቁጥራቸውን ማሳደግ፣ የዲጂታል ጤና እና በዘርፉ የተከናወኑ ልዩ ልዩ የበጎ አድራጎት ተግባራት በጤና ዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶች መሆናቸውን ሚኒስትሯ መጥቀሳቸው ለተፈጠረው አቅም ጥሩ ምሳሌ ነው። የመደመር መንግስት ለማህበራዊ ልማት በተለይም ለጤናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረት ምክንያት በርካታ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል። እነዚህ በዘርፉ የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት ለጤና ዲፕሎማሲ ዘርፍ እመርታ አበርክቷቸው ከፍተኛ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ የገለጹ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያ የተለያዩ የዘርፉ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን እንድታስተናግድ ተመራጭ እንዳደረጋት እና ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመርጣ ዓለም አቀፍ የጤና ድርድሮችንና ንግግሮችን እንድትመራ እንዳስቻላትም እንዲሁ።
የሰው ተኮር ፕሮጀክቶች እመርታ፤ የአረጋውያን በረከት፣ የታዳጊዎች የተስፋ ማዕድ
Sep 14, 2026 339
ሀገር በታሪክ ሰሪዎችና ባለውለታዎች ጀግኖች አባቶች ገድል፣ በነገ ተስፋዎች ጽናት ትገነባለች፤ በጠንካራ ተቋማትና ተስፋን በሰነቁ ፕሮጀክቶች ትጸናለች። የመደመር መንግሥት የዜጎችን ማኅበራዊና ምጣኔ-ሀብታዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከነደፋቸው ውጥኖች መካከል ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ይጠቀሳሉ። ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ፣ በተማሪዎች ምገባ እና በወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ብቻ የተመረኮዙ አይደሉም፤ ይልቁንስ የሀገር ባለውለታዎች ካስማ፣ የነገ ተስፋዎች ማገር ናቸው። የመደመር መንግሥት ማኅበራዊ ፍትሕ ማስፈን ቀዳሚ አጀንዳው ሲያደርግ፣ የትናንት የሀገር ጀግኖች ውለታ በመመለስ እና ለነገ ታዳጊዎች ብርሃን በመፈንጠቅ ነው። በኢትዮጵያ በከተማና ገጠር፣ በአዛውንቶችና ወጣቶች መካከል አንዳችም ልዩነት ሳይፈጠር የአካባቢያቸውን የመልማት ጸጋ አውጥቶ መጠቀም የሚያስችሉ የዜጎች ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ተደራሽ ሆነዋል። በትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምገባ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና የተቸረው ውጤት አስመዝግባለች፤ ሌሎች ክልሎችም ብዙ ተምረውበታል።   መንግሥት በመዲናዋ በ2018 ዓ.ም በትምህርት ቤቶች ምገባ መርሃ ግብር 976 ሺህ 702 ተማሪዎች በቀን ሁለት ጊዜ ቁርስና ምሳ መመገብ የሚያስችል ሥርዓት በማንበር ህዝባዊነቱን በተግባር ገልጧል። ሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ኢኒሼቲቩን እንደ ትምህርት በመውሰድ የትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር በመጀመር የተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ የማቋረጥ ምጣኔ ቀንሰዋል፤ የተማሪዎችን ትኩረት በመሰብሰብ ለውጤታማ መማር ማስተማር ሂደት መሰረት ጥለዋል። የደጃዝማች ወንድይራድ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ናታኒም በላይ፣ በትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር በመጀመሩ ትምህርቱን በሙሉ ትኩረት ሳያቋርጥ የሚማርበት ዕድል ማግኘቱን ገልጿል። በትምህርት ቤቶች የምገባ መርሃ ግብር መጀመሩ ለእናቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ገቢ ማግኘትና የአዕምሮ እርካታ እያገኙ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በአፄ ነአኩቶ ለአብ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች መጋቢ ወይዘሮ መሰረት እንዳለ ናቸው።   በአዲስ አበባ 30 የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም ራሳቸውን መመገብ ለማይችሉ አቅመ ደካማ ዜጎች የተመጣጠነ ምግብ የሚያገኙበት ምቹ ምኅዳር ተፈጥሯል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ 30ኛውን የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ ሲያስጀምሩ፣ የነዋሪዎችን ሕይወት ለመለወጥና ለኑሮ ምቹ አካባቢን መፍጠር ዋና አጀንዳቸው መሆኑን ተናግረዋል። የምገባ ማዕከላትን ማስፋፋት አቅመ ደካማ ወገኖችን ከመመገብ ባለፈ ለነዋሪዎቻችን ያለንን ክብር የምናሳይበትና ለዜጎች የሥራ ዕድል የምንፈጥርበት ነው ብለዋል። ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች በመዲናዋ ማኅበራዊ ፍትሕን በማንገስ የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ እንደሚያስችሉ ተናግረዋል። ሀገር ላጸኑ የሃገር ባለ ውለታዎች አባቶችና እናቶች በንጹህ፣ ጽዱና ምቹ ቤት የተደላደለ ሕይወት እንዲመሩ ተደርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ታኅሣሥ 2016 የአዋሬ መንደር የጋራ መኖሪያ ህንፃ አሰርተው ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች በአጭር ጊዜ ለውጥ የሚያመጡ፣ የዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ የሚያሻሽሉ እና ሀገር የሚያሻግሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። አዋሬን እንደ ምሳሌ በመጥቀስ፤ ዕውቀት፣ ሀብትና ጉልበት ተሰናስለው ለሀገርና ሕዝብ ካስማና ማገር የሚሆኑ ተጨባጭ ውጤቶች ማምጣት እንደሚቻል አስረድተዋል። "እንሠራለን፣ ኢትዮጵያን እንቀይራለን፣ ኢትዮጵያን እናበለጽጋለን" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ውብ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረከብ ዕድሉ በኢትዮጵያውያን እጅ ላይ እንዳለ አረጋግጠዋል። የአቅመ ደካሞችን ቤት መጠገን፣ አለፍ ሲልም አዳዲስ ምቹና ዘመናዊ የመኖሪያ መንደሮችን ከተሟላ የመንገድ፣ የውሃ፣ መብራትና መሰል መሠረተ ልማት ጋር ሰርቶ ማስረከብ የመደመር መንግሥት መገለጫ ሆኗል። በመዲናዋ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች ተሰርተው የተላለፉ ቤቶች ተጠቃሚ የሆነው ወጣት ታምራት ተመስገን የአካል ጉዳተኛ በመሆኑ በርካታ ፈተናዎችን ማስተናገዱን ገልጿል።   ይሁን እንጂ አዲስ በተረከበው ቤት እንደ ልብ መንቀሳቀስና ሕይወቱን ማሻሻል የቻለበት ዕድል እንደተፈጠረለት ገልጿል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቤታቸው የታደሰላቸው እናት ወይዘሮ ታየሁ መኮንን "ቤት ነው ለማለት እንኳን በማያስደፍር" ቤት ውስጥ ይኖሩ እንደነበር አስታውሰዋል።   በሸራና በላስቲክ ከተጠጋገነ፣ የግድግዳው አፈር ከሚናድ ቤት ውስጥ መቆየታቸውን አስታውሰው፣ "ቤቴ በመታደሱ 'ቤቱ እላዬ ላይ ይደረመሳል' ከሚል ሰቀቀን ተላቅቄ፣ ያለ ሀሳብ ጎኔን ማሳረፍ ችያለሁ" ብለዋል። በነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ከጎዳና ሕይወት ወደ ለውጥ አብነት የተሸጋገሩ ወጣት ልጃገረዶች እልፍ ናቸው። ማዕከሉ በአስከፊ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ለነበሩ ሴቶች አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ሕክምና በማድረግ፣ ዘላቂ የሕይወት ክህሎት ሥልጠና በመስጠት ሕይወታቸውን የሚያሻሽሉበት ተቋም ነው። ማዕከሉ በ2016 ዓ.ም ሥራ ከጀመረ በኋላ በአምስት ዙሮች ሦስት ሺህ 259 ሴቶችን በማሰልጠን ወጣቶች ተስፋ እንዳላቸውና ለለውጥ ቅርብ እንደሆኑ በተግባር አሳይቷል። በነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በ2018 ዓ.ም በአምስተኛ ዙር በዶሮ እርባታ ሥልጠና ወስዳ የተመረቀችው ትዕግስት ፀጋዬ፣ ማዕከሉ ከጎዳና ሕይወት ወጥታ ጠንካራ ስብዕና መገንባት የሚያስችል አቅም እንደፈጠረላት ተናግራለች።   በማዕከሉ የቤት አያያዝ ሥልጠና የወሰደችው መሰረት አበራ በበኩሏ፣ ከጎዳና ላይ ከነበረችበት አሰልቺ ሕይወት ተላቃ ጠንካራ የራስ መተማመን በመገንባት ነገን የምታልም ሴት እንዳደረጋት ገልጻለች።        
የጭስ አልባው ኢንዱስትሪ ትንሳኤ፡ የመደመር እሳቤ ትሩፋት
Sep 13, 2026 538
ኢትዮጵያ ሺህ ዘመናትን የተሻገሩ ታሪካዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶችን በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) አስመዝግባለች። በዓለም የሚዳሰስ ቅርስነት ዝርዝር ከሰፈሩ የኢትዮጵያ ቅርሶች መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የአጼ ፋሲለደስ አብያተ መንግሥታት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የሐረር ጀጎል ግንብ፣ የጢያ ትክል ድንጋይ፣ የአዋሽና የኦሞ ሸለቆዎች፣ የኮንሶ ባህላዊ መልክዓ ምድር፣ የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር፣ የራስ ዳሽንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮችና ሌሎችም ይገኙበታል።   በማይዳሰስ ቅርስነት ከሰፈሩ የኢትዮጵያ ቅርሶችም የመስቀል ደመራ በዓል፣ ፊቼ-ጫምባላላ፣ የገዳ ሥርዓት፣ ጥምቀት፣ ሹዋሊድ፣ የሶማሌ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓት፣ የወላይታ ጊፋታና የመሳሰሉት ሕያው ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊና ማኅበረሰባዊ ትውፊቶችን ያካትታሉ። እነዚህ ኢትዮጵያውያን ለዓለም ሕዝብ ያበረከቷቸው የመስህብ ሀብቶችም ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በገጽታ ግንባታና ለአካባቢ ልማት የሚያበረክቱት ዕድል በቀላሉ የሚታይ አይደለም። የመደመር መንግሥትም ይህንን የኢትዮጵያውያንን ሰፊ የቱሪዝም አቅም በመረዳት፣ ቱሪዝምን በብዝኅ ዘርፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ዕይታው ውስጥ ትኩረት ከሰጣቸው የልማት መስኮች አንዱ አድርጎታል።   በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውም ቱሪዝም ከአምስቱ የብዝኅ የኢኮኖሚ አዕማድ አንዱ እንዲሆን በመደረጉ ዘርፉ የሚያስገኘው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ የበለጠ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጓል። ይህም ዘርፉ ከነበረበት ተለምዷዊና አዝጋሚ ዕድገት የሚላቀቅበትን ዘመናዊ የቱሪዝም መዳረሻ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት፣ ነባር ቅርሶች በማደስና በመጠገን ውጤታማ ሥራ ተሰርቷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገርና በገበታ ለትውልድ የመስህብ መዳረሻ ልማት የቱሪዝሙን ዘርፍ ማንሰራራት ያበስሩ ፕሮጀክቶች እውን ሆነዋል። ለአብነትም በገበታ ለሸገር በአዲስ አበባ የተገነቡ የወዳጅነት፣ አንድነትና የእንጦጦ ፓርኮች፤ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት የመዲናዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ መቀየር ያስቻለ ምቹ ምኅዳር ፈጥረዋል።   በገበታ ለሀገርና ለትውልድ የመዳረሻ ልማት ፕሮጀክትም ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ሐላላ ኬላ፣ ደንዲ ኢኮ ሎጂ፣ አርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት፣ ሎጎ፣ ሸበሌ ሪዞርት፣ ኒን ሊ ፓልም ሎጂ እና የመሳሰሉት እንዲገነቡ አስችሏል። ይህም የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን የከተማና ገጠር የቱሪዝም መዳረሻ አሰናስሎ በማልማት ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተውን ገንቢ ሚና መወጣት የሚችልበትን ከፍተኛ ዕድል ከፍቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በቱሪዝም ጉዳዮች ላይ ከኤንቢሲ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፤ በቱሪዝም ዘርፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም መስህብ ስፍራዎች በማስፋፋትና የመዳረሻ ብዝሃነትን በማሳደግ ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በተለይም ለዘርፉ በተሰጠው ትኩረት የኢኮኖሚ መነቃቃትን በመፍጠር በሥራ ዕድል ፈጠራም ጭምር ከአምስቱ የብዝሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ማሻሻዮች መካከል አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።   በዚህም የጎብኚዎች ፍሰትን በመጨመርና የቆይታ ጊዜ በማራዘም የቱሪዝም ብዝኅ እመርታዊ ውጤቶች በየአካባቢው ኢኮኖሚን በማነቃቃት የገጠርና የከተማ ልማትን ለማስተሳሰር አዲስ ዕድል ፈጥረዋል ብለዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የመደመር መንግሥት የቱሪዝም መዳረሻ ልማትና የቅርስ ዕድሳት ውጤታማ ሥራ የዘርፉን ዳግም ውልደት ያበሰሩ ለውጦችን አምጥቷል ብለዋል። ይህም የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ጎብኝዎችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም ዘመናዊና የተሰናሰለ የከተማና ገጠር የመስህብ መዳረሻና እንቅስቃሴ እንዲፈጠር ማስቻሉን ገልጸዋል።   የቱሪዝም አስጎብኚ ድርጅቶች እንደሚሉትም፤ የኢትዮጵያ መጠነ ሰፊ የመዳረሻ ልማትና የቅርስ ጥበቃ ውጤታማ ሥራ ለቱሪስቶች መዳረሻና ጉብኝት ምቹ ምኅዳርን በመፍጠር የሀገርን ገጽታ የገለጡ ናቸው። የታላቁ የኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅቶች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት እንቁ ሙሉጌታ እንደገለጹት፤ የቱሪዝም መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪዝም ፍሰቱን በማሳደግ ተጠቃሚነትን እያሳደገ ነው።   የኤደን ላንድ ቱር ኤንድ ትራቭል ባለቤት እንዳልካቸው የምሩ፤ ለቱሪዝም ልማት የተሰጠው ትኩረት አማራጭ የመዳረሻ ስፍራዎች በማስፋፋት ለመስህብ መዳረሻ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ጎብኝዎች እንደሚሉትም፤ በኢትዮጵያ ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ ሃይማኖታዊና ተፈጥሯዊ መስህቦችን መጎብኘት የሚያስችሉ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።   ከዓለም አቀፍ ጎብኝዎች መካከል ጀርመናዊው ሉካስ ኩፕፈርናጌል፤ ኢትዮጵያ በአዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች የገነባቻቸው አስደማሚ የቱሪዝም መዳረሻዎች ሀገሪቱን አፍሪካዊት ግንባር ቀደም የቱሪስት ማዕከል የሚያደርጉ ናቸው ብለዋል።     ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ የሀገር ውስጥ ጎብኚ ምሕረት አሰፋ በበኩላቸው፤ የለሙት የቱሪዝም መዳረሻዎች የሀገርን ገጽታ የቀየሩ፣ ውብ፣ ጽዱና ዓለም አቀፍ የመስህብ ተወዳዳሪነትን የሚያጎለብቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በሃይማኖት፣ በባህልና በተፈጥሮ የታደለችውን ሀብት ወደ ኢኮኖሚያዊ አቅም የመቀየር ሥራ በስፋት እያከናወነች ይገኛል። የመደመር መንግሥት ቱሪዝምን የብዝኅ የኢኮኖሚ አዕማድ አካል በማድረግ የገነባቸው ማራኪ የመዳረሻ ስፍራዎች የዘርፉን ማንሰራራት በማጽናት ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተውን አቅም ለማጎልበት ያለመ ነው። ቀጣዩ የዘርፉ ጉዞም የኢትዮጵያን ቅርስና ተፈጥሯዊ ጸጋ በመጠበቅ የመዳረሻ ብዝኅነትን በማስፋፋትና የአገልግሎት ጥራትን በማሳደግ ቱሪዝምን ከተስፋ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ውጤት የሚያሻግር ይሆናል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦች የመቻል ተምሳሌት 
Sep 9, 2026 365
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦች የመቻል ተምሳሌት መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም የኢትዮጵያውያን የጋራ ቃል ኪዳን የታሰረባት ታሪካዊ ክስተት ናት። ዕለቷም የዓባይን የሺሕ ዘመናት ገደብ የሌለው ጉዞ በጉባ ተራሮች ግርጌ ልጓም ለማበጀት የታሰረች ቀለበት ሆና ተመዝግባለች። ኢትዮጵያውያን ቃል ኪዳናቸውን ባሰሩ ማግስት የግብፅና ሌሎች ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጩኸትና የጥፋት ሴራ በግልጽ መታየት ጀመረ። በተለይም ግብፅ ኢትዮጵያ ውስጣዊ መረጋጋት እንዳይኖራት የውስጥ ታጣቂዎችን ከመደገፍ ጀምሮ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በራፍ ጭምር የሀሰት ክሶችን እስከማሰማት የደረሰ የሺሕ ዘመናት ዓባይን በብቸኝነት የመጠቀም አባዜዋን አንጸባርቃለች። ትብብርን ከፅናት አሰናስለው የቀጠሉት ኢትዮጵያውያን ለአሥራ አራት ዓመታት የታላቁ ሕዳሴ ግድብን የማደናቀፍ የታሪካዊ ጠላቶችን ሴራ በጋራ በመመከት ለፍጻሜ አብቅተውታል። የሀገርን ሉዓላዊነት በጽናት የማስከበር የአርበኝነት ተጋድሎን ከዓድዋ ጀግኖች የወረስን እኛ ኢትዮጵያውያን በጉባ ተራሮች ግርጌ በደም፣ በላብ፣ በዕንባና በውኃ ጠብታ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን በዓባይ ላይ አንጸናል።   ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የአዲስ ዓመት ዋዜማም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በማጠናቀቅ ለፍጻሜ በማድረስ አብስሯል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሺሕ ዘመናት የልማት ጥማትን በማርካት የብልፅግና ፍኖት ብስራት ሆኗል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ለሌላ የልማት ዕቅድ ወጋገን የፈነጠቀ የንጋት ሐይቅ ፈጥሯል። ግድቡ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝቦቿ ትብብር ብቻ ያለ አንዳች የውጭ ድጋፍና ብድር ለፍጻሜ መብቃቱም ለአፍሪካውያን የመቻል ትዕምርት ሆኗል። በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ብስራት በጉባ ተራሮች ግርጌ የከተሙ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት መሪዎች የመሰከሩት ጥሬ ሐቅም ይህ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምረቃው ዕለት እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦችን የታሪክ ክብር ያደሰና ለአፍሪካውያን የመቻል ውጤት ነው። በወቅቱም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጎህ ያበሰረ፣ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርና የጋራ ዕድገት መንገድ የጠረገ ፓን-አፍሪካኒዝም ፕሮጀክት መሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ አፍሪካውያን አንጡራ ሀብታቸውን በራሳቸው አቅምና ጥረት በማልማት ታላላቅ የልማት ገድሎችን መፈጸም እንደሚችሉ ያመላከተ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የኩራት ምንጭ መሆኑንም ጠቁመዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር እና የክብር እንግዳ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ የታዳሽ ኃይል ሽግግርን በማፋጠን የአፍሪካውያንን የጋራ ምኞት የሚያሳካ ህያው ምልክት ነው ማለታቸው ይታወሳል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅና ለምረቃ መብቃትም የኢትዮጵያውያንን ለአንድ ሀገራዊ የልማት ርዕይ በጋራ የመቆም ውጤታማነትን በተግባር ለዓለም የገለጠ ፓን-አፍሪካኒዝም ፕሮጀክት መሆኑን መስክረዋል። በዚሁ ወቅት የተገኙት የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጌሌ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዘመናዊው ዓለም የአፍሪካውያን የኩራት ምንጭ የሆነ የልማት ድል መሆኑንና መላውን ዓለም ያስደነቀ የኢትዮጵያ ስኬትና የወዳጆቿ የጋራ ሀብት ነው። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ብሔራዊ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን አስደማሚ የፓን-አፍሪካኒዝም መግለጫ ፕሮጀክት ነው ያሉት ደግሞ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ የታደሙት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ናቸው።   የኢትዮጵያውያን ብሔራዊ ፕሮጀክት የሆነው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት አፍሪካውያን በተባበረ ክንድ አቅማቸውን በመጠቀም የራሳቸውን ዕድል በራሳቸው መወሰን እንደሚችሉ ትምህርት ያስተላለፈ ነው ሲሉም መግለጻቸው ይታወሳል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የምህንድስና ልህቀትም አህጉሪቱ ለብልፅግናዋ የሚረዱና ሁለንተናዊ ለውጥ የሚያመጡ ሁነኛ የልማት ፕሮጀክቶችን በራሷ አቅም የመገንባት ብቃት እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ የተገኙት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ እንደተናገሩት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አህጉራዊ ትብብርና ግንኙነትን የሚያጠናክር የወንድማማችነት ምልክት ነው። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁላችንንም ተጠቃሚ የሚያደርግ የጋራ ጉዳያችን ነው በዚህም ዕድለኞች ነን ሲሉ መግለጻቸውም ይታወሳል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ "ለእኛ እንደ አንድ ፕሮጀክት ሳይሆን ሀላፊነትን የምንጋራበት ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ አፍሪካውያን ከተባበርን ስኬቶችን ማስመዝገብ እንደምንችል ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። የላይኛውና የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት መበልጸግ የሚችሉት በጋራ እንደ አንድ ማህበረሰብ በመስራት ነው። ውሃና ሌሎች ተፈጥሯዊ ሀብቶች በድንበር የተወሰኑ ሳይሆኑ የወደፊት እጣ ፈንታችንን የሚወስኑ ናቸው ብለዋል።   የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት በበኩላችው እንደሚሉት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአንድነት እና የመስዋዕትነት ምልክት ነው። ግድቡ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን የአንድነትና የመስዋዕትነት ምልክት ነው፡፡ የግድቡ ግንባታ እውን መሆን ህዝብ ከተባበረ እና ለአንድ ዓላማ በአንድነት ከቆመ ምን መስራት እንደሚችል ማሳያ መሆኑን ነው ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህም ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የኩራት ምንጭ ነው ማለታቸው ይታወሳል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ግድቡ የኃይል ፍላጎትን ከማሳካት ባለፈ ለልጆቻችን የምንመኘውን የበለጸገ ሀገርና አህጉር ለማስረከብ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ይህ በታሪክ ድርሳናት ሰፊውን ድርሻ የሚይዘው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት የኢትዮጵያዊያን የቃል ኪዳናቸው ማህተም ሆኖ ለዘላለም ይኖራል።
ትንታኔዎች
የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ የከፍታ ጉዞ ማሳያ - ብሪክስ
Sep 13, 2026 782
''የብሪክስ ጉባዔ የጋራ ትብብርን ወደ የጋራ እሴት፣ ጽናት እና ዘላቂ ዕድገት የመለወጥ ሰፊ አቅምና ቁርጠኝነት አለው" በማለት ነው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ18ኛው የብሪክስ ጉባዔ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር። 18ኛው የብሪክስ ጉባኤ የጥምረቱ አባል ሀገራት መሪዎች በተገኙበት “ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርንና ዘላቂነትን መገንባት” በሚል መሪ ሀሳብ በህንድ ኒውዴልሂ እየተካሄደ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የልዑክ ቡድናቸው በዚሁ ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ በሚፈጥረው ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የልዑክ ቡድናቸው የብሪክስ ጉባኤ ተሳትፎ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው። ብሪክስ ለአፍሪካ ቀጣና እና በተለይም ለኢትዮጵያ በርካታ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና የጂኦ-ፖለቲካዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ አዲስ የዓለም ስርዓት እየተፈጠረበት የሚገኝ ጥምረት ነው። የብሪክስ ጥምረት ለኢትዮጵያ የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። በዚህም እንደ ቻይና፣ ህንድ እና ሩሲያ ካሉ ታላላቅ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣውን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በተለይም በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና እና በኢነርጂ ዘርፍ በማሳደግ በኩል አይነተኛ አማራጭ የኢንቨስትመንት መንገድ ነው። ጥምረቱ ለኢትዮጵያ ከሚያስገኘው ትሩፋት አንጻር ሲታይ የውጭ ምንዛሬ እጥረትን በመቅረፍ፤ ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር በሚደረጉ የንግድ ልውውጦች የሀገር ውስጥ ገንዘብን የመጠቀም ዕድልን ስለሚፈጥር፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝት እጥረትን ከመቀነስ አኳያም እንዲሁ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው። ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ዕቅዷ ኢኮኖሚዋን በመሠረታዊነት ለሚያሳድጉ መሠረተ ልማት ግንባታ እና ማስፋፊያ እንዲሁም ለቴክኖሎጂ ሽግግር ልዩ ትኩረት ሰጥታ እየሠራች ትገኛለች። ከዚህ አኳያ ብሪክስ የመንገድ፣ የባቡር፣ የኃይል ማመንጫዎችና ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና መሰል የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሚሆን የፋይናንስ ድጋፍ በማመቻቸት በኩል ኢትዮጵያ ለያዘችው ግብ ስኬት ከፍተኛ ጠቀሜታ የሚያስገኝ ጥምረት ነው። ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ላሳካቻቸው ውጤቶች የዓለም አቀፍ ግንኙነቷን የቃኘችበት አዲስ አካሄድ ተጠቃሽ ነው። ከእነዚህ ስኬቶች መካከል ደግሞ በብሪክስ ጥምረት ውስጥ አባል የሆነችበት መንገድ አንዱ ሲሆን፤ ይህ የብሪክስ ጥምረት ለኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖ ፈጣሪነት የራሱን ሚና በመጫወት ኢትዮጵያ በቀጣናው እና በአህጉሪቷ ያላትን መሪነትና ዲፕሎማሲያዊ የበላይነት በማጠናከር በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ድምፅ እንድታጎላ እና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷ እንዲያድግ እያስቻለ መሆኑም በተጨባጭ ታይቷል። የብሪክስ ጥምረት በአፍሪካ አለፍ ሲልም በጥምረቱ አባል ሀገራት መካከል ተመጣጣኝ ልማት እንዲኖር እና ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ አስቻይ ምህዳር እየፈጠረም ይገኛል። በተለይ አፍሪካ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የኢኮኖሚ ዕድገቷን እንድታፋጥን አማራጭ የፋይናንስ ምንጭ መሆን የሚያስችለውን አደረጃጀት እና አሰራር እየዘረጋም ይገኛል። ይህ የጥምረቱ አዳዲስ አደረጃጀት እና አሰራር አዲሱ የልማት ባንክ እንዲወለድ አስችሏል። በዚህ ባንክ አማካኝነት የአፍሪካ ሀገራት ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት እና ከዓለም ባንክ ጥብቅ መስፈርቶች ነፃ በሆነ መንገድ ለተለያዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አማራጭ የፋይናንስ ምንጭ ወይም ብድር እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። በጥምረቱ አማካኝነት የተፈጠረው አዲሱ የልማት ባንክ የአፍሪካ ሀገራት በራሳቸው ሀገራዊ ገንዘብ እና ከአሜሪካ ዶላር ተጽእኖ ውጪ ከታላላቅ የብሪክስ ሀገራት ጋር የንግድ ልውውጥ እንዲያከናውኑ በር እየከፈተ ይገኛል። በተጨማሪም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ የውሳኔ መድረኮች ላይ ያላትን ተፅዕኖ ፈጣሪነት በማሳደግ፣ ፍትሐዊ የሆነ የዓለም አቀፍ ስርዓት እንዲፈጠር እያስቻለ መሆኑም የአደባባይ ምስጢር ከሆነ ሰነባብቷል። ይህ የብሪክስ ጥምረት መመስረት፣ መስፋፋትና መጠናከር በዓለም የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስርዓት ላይ በርካታ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጦችንና አንድምታዎችን እያስከተለ ይገኛል። የብሪክስ ጥምረት ተመስርቶ እየፈጠረ ያለው ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ተጽዕኖ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የምዕራባውያን ሀገራት በዓለም ፖለቲካ ላይ የነበራቸውን የበላይነት በመገዳደር፣ ሥልጣንና ውሳኔ ሰጪነት ለተለያዩ የአህጉራት ኃይሎች እንዲከፋፈል፣ በዓለም አቀፍ ተቋማት ላይ የአሰራር እና የአደረጃጀት ማሻሻያ ጥያቄዎች ጎልተው እንዲሰሙ የማድረግ አቅም እየፈጠረ ነው። በተጨማሪም የብሪክስ ጥምረት አባል ሀገራት በንግድ ልውውጣቸው ወቅት በራሳቸው ሀገራዊ ገንዘቦች የመጠቀም ዝንባሌያቸው በመጨመሩ፣ የአሜሪካ ዶላር በዓለም ንግድና መጠባበቂያ ክምችት ላይ ያለውን ፍጹም የበላይነት በማዳከም፤ አዲሱ ልማት ባንክ የብሪክስ የድንገተኛ የገንዘብ ድጋፍ ማዕቀፍ የምዕራባውያኑን ጥብቅ የፖለቲካ መስፈርቶች ሳይከተሉ ለታዳጊ ሀገራት ፕሮጀክቶች ፋይናንስ እንዲያቀርቡ ብሎም የብሪክስ አባል ሀገራት የዓለምን ከፍተኛ የነዳጅ፣ የጋዝ፣ የብረታ ብረት እና የግብርና ምርቶች አቅርቦት የሚቆጣጠሩ በመሆናቸው፣ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች እና የዋጋ ውሳኔዎች ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ የውሳኔ ሰጪነት አቅማቸውን እያሳደገ መጥቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያም ሆነች አፍሪካ ያላቸውን የመልማት አቅም ለመጠቀም አማራጭ የልማት ፋይናንስ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል። ለዚህ ደግሞ የብሪክስ ጥምረት ይዞት የመጣውን ዕድል በውል አንስተዋል። ለዚህም ነው በብሪክስ አባል ሀገራት ዘንድ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ እና ሰፊ ገበያ አለን፤ አሁን ያለው መልካም ዕድል እነዚህን አቅሞች በማስተሳሰር የላቀ እሴት መፍጠር እና ይህ እሴት ደግሞ ሀብቱ በሚገኝበት ቦታ መመረት እንዲችል ማድረግ ነው ሲሉ ያመላከቱት። ኢትዮጵያ በማዕድን ልማት፣ በታዳሽ ኃይል እና እያደገ በሚገኘው የኢንዱስትሪ መሠረቷ ላይ እነዚህን አጋርነቶች ለመገንባት ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በአሠራር ሥርዓቶቻችን ውስጥ ጽናትን መገንባት፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የአህጉራችንን ፍላጎት እንዲያገለግል ማድረግ፣ አስተማማኝ የዕዳ እፎይታ ሒደትን ማሳደግ እንዲሁም የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራዎችን ከኢኮኖሚ ሽግግር ጋር ማስተሳሰር ከጥምረቱ የሚጠበቅ መሆኑንም ነው ያነሱት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የብሪክስ ጉባዔ የጋራ ትብብርን ወደ የጋራ እሴት፣ ጽናት እና ዘላቂ ዕድገት የመለወጥ ሰፊ አቅምና ቁርጠኝነት አለው። የጥምረቱ አቅም ከተናጠል አካሄድ ይልቅ ትብብርና ለጋራ እሴት መጎልበት ያለውን ዕድል ያመላክታል። ኢትዮጵያ ለኮቪድ እና ኤልኒኖን ጨምሮ ለዓለም የኢኮኖሚ እና የንግድ ስርዓት መመሰቃቀል እጅ ሳትሰጥ፤ ይልቁንም መሰል ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ችግሮችን ወደ ዕድል በመቀየር፤ ለችግሮች የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ባከናወነቻቸው ተግባራት ጽናትን ገንዘቧ እያደረገች ትገኛለች። ለዚህም ነው "አካታች ዓለም አቀፍ አስተዳደር እና ባለ ብዙ ወገን ትብብርን ማጠናከር” በሚል አጀንዳ ላይ ትኩረት ባደረገው የጉባኤው የመጀመሪያ ቀን ውሎ ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ችግሮች ከመፈጠራቸው አስቀድሞ ጽናትን ማጠናከር እና የአስተዳደር ስርዓት አካል የማድረግን መሠረታዊ ጠቀሜታ የገለጹት። ይህ ጽኑ ስርዓት ግንባታ ኢትዮጵያ በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ እንድትበረታ ማስቻሉን ለማሳያነት አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ከውጭ ከሚገባ የስንዴ ጥገኝነት ተላቃ በምግብ ራሷን መቻሏን አንስተዋል። በጤና ቅድመ መከላከል ፖሊሲ አካል ሆኖ የሕክምና ቁሳቁሶችና መድኃኒቶች ማምረትን፣ የዲጂታል ስርዓት ሽግግርንና ደኅንነቱ የተጠበቀ አጠቃቀም የማስፈን አበይት ተግባራት መከናወናቸውን ነው አጽንኦት የሰጡት። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የጀመረችው የመደመር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ አፍሪካ የነገውን የቴክኖሎጂ ዘመን በባለቤትነት እንድትመራ ትልቅ ሚና የሚጫወት መሆኑን የገለጹት። በእነዚህና መሰል የልማት ትብብሮች ከጥምረቱ አባል ሀገራት ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኗንም ነው ያረጋገጡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ጥምረቱ የተቋቋመበትን ዓላማ እና መርህ በተጨባጭ እውን እያደረገች እንደምትገኝ በመጠቆም፤ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ስርዓት ማሻሻያ ባከናወነቻቸው አመርቂ ትግበራዎች፣ በታዳሽ ኃይል መስፋፋት እና የኢንዱስትሪ መሠረት ልማቶቿ፣ በግብርና ስርዓት ማሻሻያ እየተመዘገቡ ያሉ የምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ ብሎም ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ግዙፍ የአየር መንገድ ግንባታ የአኅጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ንግድ ትሥሥርን ለማስፋፋት በምታደርገው ጥረት በጥምረቱ ለሚነሱ ተያያዥ የውይይት አጀንዳዎች መሪ ተዋናይ መሆን እንደሚያስችላትም አንስተዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የልዑክ ቡድናቸው የብሪክስ ጉባኤ ተሳትፎ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው መሆኑ እሙን ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው እያደረጉት ካለው ተሳትፎ ጎን ለጎን ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ትብብሮችን በሚያጠናክሩ አጀንዳዎች ላይ ከተለያዩ የብሪክስ ስብስብ አባል ሀገራት መሪዎች ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል። በዚህም ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን፣ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ፣ ከቪየትናም ጠቅላይ ሚኒስትር ሌ ሚን ሁንግ፣ ከካዛኪስታን ፕሬዚዳንት ቃሲም ጆማርት ቶካዬቭ፣ ከአቡ ዳቢ አልጋ ወራሽ ከልዑል ሼህ ኻሊድ ቢን ሙሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያ፣ ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም፣ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያ እንዲሁም ከሌሎች መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ትብብርን በሚያጠናክሩ አጀንዳዎች ላይ ውጤታማ ውይይቶችን አካሂደዋል። የውይይቶቹ ማጠንጠኛም የጥምረቱን አባል ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያበረታቱ እንደ ኢንቨስትመንት፣ ቀጣናዊ ጉዳዮች፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የአቅም ግንባታና ክህሎት፣ ቱሪዝም፣ የማዕድን ልማት እና ወደ ኮፕ 32 በሚደረገው ጉዞ ላይ ሊኖሩ ስለሚችሉ ትብብሮች ላይ ያተኮሩ እንደነበሩ ተመላክቷል።
ከታሪክ ዘካሪነት ወደ ታሪክ ሰሪነት፤ የአዲሱ ትውልድ የሜጋ ፕሮጀክቶች ግንባታ አብዮት
Sep 13, 2026 506
የአንድ ሕዝብ የነፃነት ድል የሚያበቃው በድል ማግስት በሚተረክ የታሪክ መዛግብት ብቻ አይደለም። በሌላ የታሪክ ገጽ ላይ አዲስ ድል መጎናፀፍ ሲቻል የቀደመውን ድል ትርጉምና ምልዑነት የበለጠ ያጎላዋል። ዓድዋ የክንደ ብርቱ ቅድመ አያቶች የሀገርን ሉዓላዊ ነፃነት የማስጠበቅ አኩሪ የድል ምልክት ነው። የድል ምልክትነቱም ለጭቁኑ የዓለም ጥቁር ሕዝቦች ፅናትና የነፃነት ጎህን በመቅደድ፣ ለአሁኑ ትውልድ ደግሞ የይቻላል መንፈስን አጎናፅፏል። ጀግንነትንና አልበገር ባይነትን ከቅድመ አያቶቹ የወረሰው የአሁኑ ትውልድም በሌላ የታሪክ ገጽ በጉባ ተራሮች ግርጌ በዓባይ የዘመናት ዥረት ላይ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመገንባት የራሱን ታሪክ ጽፏል።   የሕዳሴ ምረቃ የተበሰረባት ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ዕለትም የኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌትነት የሚበይኑ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የተበሰሩባት ድርብ ታሪካዊት ዕለት ሆና ተመዝግባለች። በሕዳሴ የይቻላል መንፈስን የተጎናፀፈችው ኢትዮጵያም በኃይል፣ በግብርና፣ በአቪዬሽን፣ በጋዝ፣ በማዕድንና በሌሎች ዘርፎች ወደ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተሸጋግራለች። የጉባ ብስራቶችም የአንድ ፕሮጀክት ወይም ዘርፍ ስኬት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ሀብቷን በራሷ አቅም በማልማት የብልፅግና ጉዞዋን ለማስፋት የምታደርገው የልማት ጉዞ ሕያው ምልክት ናቸው። የመደመር መንግሥት አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት ኢትዮጵያን በራሷ ልጆች የመቅረጽ ራዕይም ከዓድዋ ነፃነትን፣ ከሕዳሴ የልማት ድልን፣ ከጉባ ተራሮች ግርጌ ብስራትን በመሰነቅ ታሪክን ከመዘከር ወደ አዲስ ታሪክ መጻፍ ተሸጋግሯል። ይህም ሕዳሴ ግድብ በአንድ የታሪክ ምዕራፍ ብቻ ተከትቦ የሚቀር የትውልድ ዓርማ ሳይሆን ለሚቀጥሉት ትውልዶች የመፈጸም አቅምና የይቻላል መንፈስ የሚያስተላልፍ ቅርስ መሆኑን ያሳያል። የአንድ ግዙፍ የትውልዱ ብሔራዊ ፕሮጀክት ምረቃም የሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶችን ውልደት በማብሰር ኢትዮጵያ በአዲስ የስኬት ምዕራፍ እየተስፈነጠረች መሆኗን ያመላክታል። የጉባ ብስራት የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ፣ የጋዝ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የማዳበሪያ ፋብሪካዎች፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ እንዲሁም የ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ አብነቶች ናቸው። ኃይልን ከግብርና፣ ኢንዱስትሪን ከአቬየሽን ያሰናሰሉት የጉባ ብስራት ግዙፍ ፕሮጀክቶችም በዚህ የልማት ጉዞ ቀጣዩን ምዕራፍ መጻፍ ጀምረዋል። ይህም ኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶችን የምታልም ሀገር ብቻ ሳትሆን የመፈጸም አቅም ያላት መሆኗን የሚያሳይ አዲስ የልማት ምዕራፍ ነው። በመደመር መንግሥት ውልደት ማግስት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና በፖለቲካዊ ዘርፎች ያስመዘገበቻቸው እመርታዎች ሀገርን ከመዋቅራዊ ስብራት ወደ ማንሰራራት ያሸጋገሩ ድሎች ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ታሪካዊቷ ዕለት እንዳሉት፤ ሕዳሴ ያስገኘው ወኔና ተስፋ የነገዋን ኢትዮጵያ ብሩህ አድማስ የሚያበስሩ ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም መንገድ ከፍቷል። በዚህም በጥቂት ዓመታት ውስጥ ለሰላማዊ ዓላማ የሚውል የኒውክሌር ፕላንት፣ የጋዝ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካዎች፣ እንዲሁም 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን የመኖሪያ ቤቶች እንደሚገነቡ ማብሰራቸው ይታወሳል። እነዚህ ግዙፍ የልማት ዕቅዶች በቁጥር የሚገለጹ ፕሮጀክቶች ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን ከራሷ የመፈጸም አቅም ጋር በማሰናሰል የነገን ሀገራዊ ተስፋ የሚያመላክቱ የልማት አቅጣጫዎች ናቸው። የመደመር መንግሥት ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ትልሞችም የኢትዮጵያን ሁሉን አቀፍ የማንሰራራት ምዕራፍ በማብሰር፣ የሀገርን ብልፅግና የሚቀርጹ እመርታዎች የተገኙባቸው ናቸው። ከእነዚህ መካከል የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአየር ማረፊያ የፕሮጀክት ግንባታ ብስራት አንዱ ነው። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፍ ያላትን አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በማጎልበት፣ በኢኮኖሚ፣ በቱሪዝምና በዲፕሎማሲ ዘርፎች አዳዲስ ዕድሎችን የሚከፍት ቁልፍ መሠረተ ልማት ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፕሮጀክቱን ግንባታ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ዘርፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ ነው። በዚህ መነፅር ሲታይም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአየር ማረፊያ ፕሮጀክት የአቪዬሽን ፕሮጀክት ብቻ አይሆንም። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ያላትን የአቪዬሽን መሪነት በማላቅ፣ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን የሚያጎለብት ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ይሆናል። የቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ግዝፈትና ዝማኔ ኢትዮጵያን የአቪዬሽን፣ የቱሪዝምና የዲፕሎማሲ ማዕከል የማድረግ ከፍተኛ አቅም አለው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ናቸው። ይህም ሕዳሴ ግድብ ያስተዋወቀው የታላቅ ሀገር ግዙፍ ፕሮጀክትን የመፈጸም ባህል ከኃይል ዘርፍ ወደ አቪዬሽንና ሌሎች ስትራቴጂካዊ የልማት መስኮች እየተስፋፋ መሆኑን ያመላክታል። ሌላኛው የኢትዮጵያን የማንሰራራት አቅጣጫ የሚበይነው ግዙፍ ፕሮጀክትም የተፈጥሮ ጋዝና የአፈር ማዳበሪያን በሀገር ውስጥ የማምረት ትልም ነው። የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብት ከመሬት ሥር ተደብቆ የሚቀር ሳይሆን፣ የምርት፣ የኢንዱስትሪና የኢኮኖሚ ልማት መሠረት የማድረግ አዲስ የዕድገት አቅጣጫ ሆኗል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክትን ባስጀመሩበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ የጋዝ ምርት ፕሮጀክት የኃይል አቅርቦትን ከግብርና ምርታማነት ጋር ያሰናሰለ ነው ብለዋል። ይህም የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ የኃይል አቅርቦትን ከማሟላት ባሻገር፣ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጉዞ በስፍራው ለሚገነባው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግብዓትነት ያገለግላል። በዚህ አተያይም ጋዝን ማልማት የኃይል ፍላጎትን ከማሟላት ባሻገር፣ የግብርና ምርታማነትን፣ የኢንዱስትሪ ምርትንና የሀገር ውስጥ ግብዓት አቅርቦትን የሚያጠናክር የተሰናሰለ ስልታዊ የልማት አቅም ይፈጥራል። የመደመር መንግሥት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ለብዝኅ ክፍለ ኢኮኖሚ ዕድገት የሰጠው ትኩረትም ኢትዮጵያን በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና ዲጂታል ዘርፎች በስኬት ምሕዋር እንድትገባ አድርጓታል። ይህም የኢትዮጵያን ማዕድን ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ እሴት የታከለበትና ፈጠራ ያለበት የምርት ሰንሰለት የሚሸጋገርበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል።   የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ፣ የካሉብ ፋብሪካ የተፈጥሮ ጋዝ ማጣራትና ወደ ፈሳሽነት የመቀየር የማዕድን ልማት ለተሽከርካሪና ፋብሪካ አማራጭ የኃይል ምንጭ ማቅረብ የሚያስችል ነው ብለዋል። ይህ ተፈጥሮ ሀብትን በጥሬ ዕቃነት ከመሸጥ ይልቅ በማቀነባበርና በማልማት የበለጠ እሴት ለማስገኘት የተያዘውን አቅጣጫ ያመላክታል። የመደመር መንግሥት ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያም የግሉን ዘርፍ በማሳተፍና ዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን በመሳብ፣ አዳዲስ የልማትና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ከፍቷል። ለዚህም ነው የዳንጎቴ ግሩፕ ባለቤትና መሥራች አሊኮ ዳንጎቴ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም በኢኮኖሚው ውስጥ ጤናማ ውድድርና ቀልጣፋ አሠራር እንዲፈጠር አድርጓል ብለዋል። ከሕዳሴ ግድብ እስከ አቪዬሽን፣ ከተፈጥሮ ጋዝ እስከ ማዳበሪያ ድረስ ገሃድ የገለጠው የኢትዮጵያ ማንሰራራትም ከማለም ወደ መፈጸም፣ ከመፈጸምም ወደ ዘላቂ የልማት አቅም ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ ያመላክታል። የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውያንን አንድነትና የጋራ አቅም ለዓለም ታሪክ ያሳየ ድል እንደነበር ሁሉ፣ ሕዳሴ ግድብም ያንኑ የጋራ አቅም በዘመናዊ ልማት ላይ የገለጠ አዲስ ታሪካዊ ክስተት ሆኗል። የኢትዮጵያውያን አንድነት የዓድዋን ድል ካቀዳጀ፣ ያው በሕብር የተሸመነ አንድነትም ሕዳሴን እውን አድርጓል። ሕዳሴ የተስፋ ብርሃን ካበራ፣ ያ ተስፋም በሌሎች የልማት ሜጋ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ሆኖ እየቀጠለ ነው። ይህ የይቻላል መንፈስ ከፕሮጀክት ወደ ፕሮጀክት የሚጓዝ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያውያን ስለነገ ሀገራቸው ያላቸውን እምነት የሚያድስ የልማት ብስራት ነው። ሕዳሴ ግድብ የተጀመረውን የተስፋ ጉዞ አዲስ አቅጣጫ አስይዞታል። የሚቀጥለው ታላቅ ተግባር ደግሞ ይህን የመፈጸም አቅም ወደ ዘላቂ ምርታማነት፣ የሥራ ዕድል፣ የዜጎች ተጠቃሚነትና የተሻለ ኑሮ መቀየር ነው። እናም የሕዳሴ ግድብ ብስራት በግድቡ የውሃ ሙሌት ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ በኢትዮጵያውያን የጋራ ህልም፣ በሀገራዊ አንድነትና በመፈጸም አቅም የሚቀጥል የልማት ብስራትን ፈንጥቋል።    
የዲጂታል አብዮት ለነገዋ ኢትዮጵያ
Sep 9, 2026 443
በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ የዛሬን ፈታኝ ሁኔታዎች ከመቅረፍ ባለፈ፣ ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር በፍጥነት እያሸጋገራት ይገኛል። የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታዎች እና የተቋማት ማጠናከሪያ ስራዎች ለዚሁ አገራዊ የነገ ትራንስፎርሜሽን በምሳሌነት የሚጠቀሱ ዋና ዋና እርምጃዎች ናቸው። መንግስት የዲጂታል ዘርፉን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሶሶ በማድረግ የነደፈውን "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ስትራቴጂ በስኬት ማጠናቀቁ፣ 2030 ዲጂታል ስትራቴጂን መጀመሩ ሀገሪቱን በቴክኖሎጂው ዘርፍ ወደ አዲስ የወደፊት ምዕራፍ እንድትገባ ያስቻለ መሰረታዊ ለውጥ አምጥቷል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ፣ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም መዘመን ለኢንተርኔት ተደራሽነት መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። በተለይም የ5G ቴክኖሎጂ አገልግሎት በስፋት መጀመሩ ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ በቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትና በመሰረተ ልማት ዝግጁነት ቀዳሚ ያደረጋት ሲሆን፣ ይህም ለነገው ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እና ለቀጣይ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቱ መዘመን በፋይናንስ ዘርፉ ላይ አብዮታዊ ለውጥ በማምጣት የነገዋን ስማርት ኢኮኖሚ መደላደል ጥሏል። እንደ ቴሌብር ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ ለአካታች ዲጂታል ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም ሆነዋል። ይህ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ምህዳር መስፋፋት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የዲጂታል ክፍያዎችን እንዲቀበሉና የፋይናንስ ተደራሽነታቸው እንዲያድግ ያስቻለ ሲሆን፣ መደበኛ ያልሆነውን የግብይት ስርዓት ወደ ዘመናዊና ግልጽ የነገ ዲጂታል ስርዓት የመቀየር ሂደቱን አፋጥኖታል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የኢትዮጵያ ሰውሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም የሀገሪቱን ታላቅ የነገ ራዕይ ለዓለም አሳይቷል። ኢንስቲትዩቱ በጤናው ዘርፍ የካንሰርና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ የሚያውቁ የኤአይ ውጤቶችን በማበልጸግ ህይወትን የማዳን ስራ እያከናወነ ይገኛል። በተመሳሳይ በግብርናው ዘርፍ የአፈር ለምነትንና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም ለነገዋ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥና ለምርታማነት ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ የለውጡ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል አለም ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱ በማድረግ ለነገው ትውልድ የባህል እና የእውቀት መተላለፊያ ምቹ መንገድ ፈጥሯል። ከዚሁ ጎን ለጎን የ"ፋይዳ" (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት የዜጎችን መረጃ በማደራጀት ለነገው ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ አስተማማኝ የመረጃ መሰረት ጥሏል። ይህም ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ቀልጣፋ አሰራርን ፈጥሯል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የነገዋን አሰራር ዛሬ ማሳያ ሲሆን፣ የሳይንስ ሙዚየም ደግሞ የነገዎቹን ፈጣሪዎች አቅም የሚያበለጽግ ማዕከል ሆኗል። በተጨማሪም በዲጂታል ክህሎት ግንባታ ረገድ ለወጣቶችና ለባለሙያዎች የሚሰጡ የስልጠና ፕሮግራሞች በስፋት እየተካሄዱ ይገኛሉ። ይህም ኢትዮጵያ በነገው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መድረክ ብቁ እና ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ኃይል እንድታፈራ ዘላቂ መሰረት እየጣለ ነው።
ነገን በብልሃት ማነጽ - የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ
Sep 9, 2026 355
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የጀመረችውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አጠናክራ ለመቀጠል እና ከጊዜው ፈጣን የቴክኖሎጂ እድገት ጋር ለመራመድ “የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂን በይፋ አድርጋለች። ታኅሣሥ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው ይህ ታላቅ አገራዊ ዕቅድ፤ ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዓለም ከተመልካችነት ይልቅ ተሳታፊና መሪ የምትሆንበትን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው። ይህ አዲስ ስትራቴጂ ከቁጥሮች እና ከኢኮኖሚያዊ ስኬቶች ባሻገር፣ ዛሬን ከመቅረጽ ባለፈ ነገን ከመገንባት እና ለቀጣይ ትውልድ አሻራ ከማስቀመጥ አንጻር ሰፊና ጥልቅ ፋይዳ ያለው ሀገራዊ ትልም ነው። በዲጂታል ዘመን የመረጃ ሉዓላዊነት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው ። በዚህ ዘርፍ የሚያጋጥም ጥገኝነት የሃገር ደህንነት ላይም የራሱን አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳረፉ አይቀርም። ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዚህ ዙሪያ መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ ነው ማለታቸው ይታወሳል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነውም ብለዋል። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ከወረቀት ባለፈ በህዝብና በሀገር ላይ የሚኖረው ተጨባጭ ማሳያ በአጭር ጊዜ ውስጥ መሬት የረገጠ እውነታ ነው። ለአብነት ያህል፣ በዓለም ሁለተኛውና ለአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ግንባታ መጀመሩ እና ከዩኤንዲፒ ጋር በመተባበር የተመረቀው 'AI UniPod' ማዕከል ለወጣቶች የተፈጠረ ትልቅ የቴክኖሎጂ መሠረት ነው። ተቋማቱ ከሀገር ውስጥ አልፎ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል በማመቻቸት ላይ መሆናቸው፣ ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የፈጠራ ማዕከል ሆና እንድትቀጥል የሚያስችላት የትውልድ አሻራ ነው። የሞባይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር 128 ሚሊዮን ለማድረስ እንዲሁም የ5G ኔትወርክ ተደራሽነትን ሙሉ በሙሉ እውን ለማድረግ የተነደፈው ዕቅድ፣ በከተማና በገጠር መካከል የነበረውን የዲጂታል ክፍተት በማጥበብ የመረጃ እኩልነትን የሚያረጋግጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው። እንደ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከመሳሰሉ መሠረተ ልማቶች ጋር ተቀናጅቶ የሚሰራው ይህ እቅድ፣ የዜጎችን ተደራሽነት በማስፋት እኩል እድል የሚፈጥር አሰራርን ይዘረጋል። ይህ የዲጂታል መረብ መስፋፋት የዜጎችን ኑሮ በጥራት ከማሻሻል ባለፈ አገልግሎቶች በፍጥነት እንዲቀላጠፉ ትልቅ አቅም ይፈጥራል። የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ ለማድረግ የሚከናወነው አሰራር ግልጽነትን በማስፈን በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመንን ያጎለብታል። ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የዛሬን ስኬት ብቻ ሳይሆን የወደፊቱን ትውልድ አዕምሮ በዕውቀትና በፈጠራ ብርሃን በመቅረጽ የሀገርን የሰው ሀብት በዘላቂነት የሚያለማ የዕድገት ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው ካነጣጠረባቸው ቁልፍ ነጥቦች መካከል ተደራሽነትን ማስፋት፣ እኩል እድል መፍጠር እና በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ይገኙበታል። ግልጽነት የሰፈነበት፣ ከወረቀትና ከቢሮክራሲ የጸዳ አሰራር መዘርጋቱ ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ላይ ያላቸውን እምነት ያጠናክራል። ይህ ደግሞ ማህበራዊ መተሳሰርን አጠናክሮ ለአንድነትና ለጋራ ብልጽግና መሰረት የሚጥል ትውልድ ተሻጋሪ ስራም ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ሥራ ዕድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት የወጣቶችን ፈጠራ ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም መቀየር ያስችላል። ወጣቱ በዲጂታል ንግድ፣ በሶፍትዌር ልማት እና በዲጂታል አገልግሎቶች ላይ ተሰማርቶ በራሱ ጥረት እያደገ ሲሄድ፣ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ መሠረት የጸና ይሆናል። የዲጂታል ኢኮኖሚ እያደገ ሲሄድ የሳይበር ደህንነት እና የመረጃ ጥበቃ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የሳይበር ደህንነት መሠረተ ልማቶችን ማጠናከሩን እንደ ዋና ዕቅድ ይዞ መንቀሳቀሱ ዜጎችና ተቋማት በአስተማማኝ ዲጂታል ምህዳር ውስጥ እንዲኖሩ ያስችላል። ቴክኖሎጂ የሉዓላዊነት ሌላኛው መገለጫ በመሆኑ፣ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማትን ማስፋት ወሳኝ ነው። መረጃዎች በውጭ አካላት ቁጥጥር ስር ሲሆኑ የሀገር ደህንነት አደጋ ላይ ይወድቃል። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የመረጃ ደህንነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የሚያስችል አቅም በመፍጠር ለነገው ትውልድ የባለቤትነት ስሜት ያጎናጸፋል። ወጣቶች በሮቦቲክስ፣ በዳታ ሳይንስ እና በሶፍትዌር ልማት ላይ ሲሰማሩ፣ ችግሮችን በፈጠራ ሃሳብ የሚፈቱ አዳዲስ ጅምሮች ይፈጠራሉ። ይህም የወጣቱን የእውቀት አቅምና ክህሎት ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ ውጤት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ ራሱን የቻለ የኢኮኖሚ መሠረት ይጥላል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ስኬት ከተቀናጀ የመደመር እሳቤ ጋር የሚተሳሰር ነው። ነገን የተረጋጋ ሰላምና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና የምናረጋግጥበት ሁነኛ መንገድም ጭምር ።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 13257
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 22449
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 15473
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 21220
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 106887
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 80750
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 59071
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 56678
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 40355
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 40270
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 39721
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 38204
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 106887
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 80750
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 59071
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 56678
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በሕብር የተሸመነ አንድነት፤ የኢትዮጵያ ጥንካሬ የወል እውነት
Sep 15, 2026 217
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):-በሕብር የተሸመነ አንድነት፤ የኢትዮጵያ ጥንካሬ የወል እውነት የኢትዮጵያ የረጅም ዘመናት የሀገረ መንግሥት ግንባታ የታሪክ ምዕራፎች ከዜጎቿ በሕብር የተሸመነ አንድነት የሚመነጭ ነው። በዚህ የረጅም ዘመናት የታሪክ ጉዞም የኢትዮጵያውያን ብዝኅ ማንነቶች፣ ቋንቋዎች፣ ሃይማኖቶች፣ ባሕሎችና ልዩ ልዩ እሴቶች በአንዲት የኢትዮጵያ ማዕቀፍ ሥር ተሳስረውና ተሰናስለው የዘለቁ ውድ ሀብቶች ናቸው። የኢትዮጵያውያን በሕብረ ብሔራዊ አንድነት የተሸመነ እውነትም ከሀገር መለያነት ባሻገር በዜጎች መካከል ለዘመናት የተገነባ የጋራ ሕይወት ውጤት ነው። በሕብር የተሸመነው ይህ ማኅበራዊ እሴት በልዩነት ውስጥ የእኛነት፣ በብዝሃነት ውስጥ የአንድነት፣ በተለያዩ ማንነቶች ውስጥ የኢትዮጵያዊነት የጋራ እሴት አሸብርቆ ይታያል። ይህን የጋራ እውነት በማጠናከር ለቀጣዩ ትውልድ ማሸጋገርም በራሱ መንገድ ብቻ የሚፈጸም አይደለም። የጋራ ታሪክ፣ እሴትና ሀገራዊ ምልክትን በማስተሳሰር አሰባሳቢና የጋራ ትርክትን መገንባትም ይጠይቃል። የአሰባሳቢ ትርክት ግንባታ የተለያዩ ማንነቶችን ማጥፋት ሳይሆን፤ በልዩነቶች መካከል የጋራ እሴቶችን በማጉላት ለአንድ ሀገራዊ ዓላማ መሰለፍ የሚያስችል ቀጣይነት ያለው የአስተሳሰብ ውቅር ነው። በዚህ ሂደት የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የጋራ ታሪካቸውን በመረዳት፣ የጋራ እሴቶቻቸውን በማጎልበትና የጋራ የወደፊት ራዕይን በመጋራት ከእኔ ወደ እኛ የሚያመራ ሀገራዊ አስተሳሰብን ያጎለብታሉ። ለዚህም ሀገራዊ ምክክር ጉልህ ሚና አለው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤም ለዘመናት የተስተጋቡ የአለመግባባት ትርክቶችን በአሳታፊና አካታች የሃሳብ የበላይነት ለማረቅ ሁነኛ መሰረት ጥሏል። የምክክር ጉባኤው ምክረ ሃሳብ ውጤቶችም የመቀራረብና የአንድነት መንፈስን በማጎናጸፍ ኢትዮጵያውያን ቀጣይነት ላለው ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚተባበሩበትን ታሪካዊ ዕድል ፈጥሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምክክር ጉባኤ ማስጀመሪያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ምክክር ከእኔነት ወደ እኛነት ሀገራዊ ማዕቀፍ የሚያመራ ሁነኛ የአሰባሳቢ ትርክት ግንባታ መንገድ ነው ብለዋል። የምክክር ጉባኤውም ለሀገርና ለጋራ ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት የጋራ ሀገራዊ አስተሳሰብን ለማጠናከር መሰረት የሚጥል መሆኑን አስገንዝበዋል። የምክክር መድረኩም የታሪክን፣ የአጋጣሚንና የዕድልን ማዝለቀቅ ለፈለጉ ሰዎች፤ በዚያ ብዕርና ብራና ላይ ሀገርን የሚታደግ፣ የሚገነባና ለዘመናት የሚታወስ ታሪክ ለመጻፍ ዕድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ይህም ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የምክረ ሃሳብ ውጤቶች ከአንድ የምክክር መድረክ በላይ ለጋራ ሀገራዊ እሴትና የወደፊት ራዕይ ግንባታ ወሳኝ ዕድል የሚፈጥር ታሪካዊ ሂደት መሆኑን ያመላክታል። ኢትዮጵያ በሕዝቦቿ አንድነትና ትብብር የጋራ ታሪክን ወደ የጋራ የወደፊት ራዕይ ለመለወጥ የሚያስችሏት በርካታ አጋጣሚዎችን ያሳለፈች ታላቅ ሀገር ናት። ከእነዚህ መካከል የዓድዋ ድል አንዱ ምልክት ነው። የዓድዋ ድል በአንድ ዘመን በተፈጸመ ወረራ ላይ የተገኘ ወታደራዊ ድል ብቻ አይደለም። በሕብር የተሸመኑ ኢትዮጵያውያን የሀገርን ሉዓላዊ ነጻነት ለማስጠበቅ በአንድ ዓላማ የተሰለፉበት የጋራ ታሪካዊ የወል እውነት ነው። የዓድዋ ድል በኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት የደምና አጥንት መስዋዕትነት ደማቅ ቀለም ተሸምኖ የተጻፈ የነጻነት ታሪክ ነው። በዚህ የታሪክ ገጽ የግል ልዩነቶቻቸውን በይደር የያዙ ኢትዮጵያውያን የሀገርን ጥቅም ከግል ጥቅም በተሻገረ ዕይታ በመመልከት ከአራቱም ማዕዘናት ለጋራ ዓላማ ተሰልፈው ድልን የተጎናጸፉበት ክስተት ሆኗል። ይህ የዓድዋ ትርክት ለዛሬው ትውልድ የሚያስተላልፈው ዋና መልዕክትም የሀገርን ጉዳይ በማስቀደም ለጋራ ዓላማ መሳካት ሕብረ ብሔራዊ አንድነት የተሸመነ ሀገራዊ ትብብር ወሳኝ አቅም መሆኑን ነው። የዓድዋ አርበኝነትን በልማት የትብብር መንፈስ የተላበሰው አዲሱ ትውልድም በጉባ ተራሮች ግርጌ በፈጸመው ታላቅ ገድል ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመገንባት የራሱን ታሪክ ጽፏል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫም በትብብር፣ በመደጋገፍና በዜጎች የጋራ ርብርብ የተገነባ መሆኑ የዘመኑና የቀጣይ ትውልድ የጋራ ሀገራዊ አሰባሳቢ ትርክት መገንቢያ ፕሮጀክት ለመሆን በቅቷል። በፕሮጀክት ግንባታ ሂደትም የአራቱም ማዕዘናት የኢትዮጵያ ሕዝቦች ያላቸውን በማዋጣት በጋራ ተሰልፈዋል፤ የሀገር ጉዳይ ሲሆን የጋራ ዓላማ ልዩነት እንደማይገድባቸውም በተግባር አስመስክረዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ በትርክት መዛባት ምክንያት የበዙ ውድ ዋጋዎችን ስትከፍል መቆየቷን አስታውሰዋል። በዚህም የመደመር መንግሥት የትናንት ቁርሾዎችን በንግግር፣ በውይይትና በምክክር መፍትሔ በመስጠት አሰባሳቢና የወል ትርክትን ለመገንባት የሚያስችል መሰረት መጣሉን አስገንዝበዋል። ለዚህም እኩልነትን፣ አካታችነትንና አሳታፊነትን ማዕከል ያደረገ አሰባሳቢና የወል ትርክት እየተገነባ መሆኑን አጽንኦት የሰጡት። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በበኩላቸው፤ ንዑሳን፣ አካባቢያዊ፣ ተቋማዊና ሌሎች የትርክት ዓይነቶች የሰው ልጆች ጠባይና ተፈጥሯዊ መሆናቸውን ገልጸዋል። ንዑሳን ትርክቶችንም ሀገር እንደ ትምህርትና ፕሮጀክት በማድረግ ልታበረታታቸው አይገባም ያሉት አማካሪ ሚኒስትሩ፤ የሀገር መሰረታዊ ማዕከል የወል እውነት ነው ብለዋል። በሀገር ደረጃ ሁሉንም የሚያስተሳስር የወል ትርክት ቀዳሚ ሊሆን እንደሚገባ ማስገንዘባቸውም አስተሳሳሪ ትርክት ግንባታ ትኩረት የሚሻ መሆኑን አስረጂ ነው። ኢትዮጵያ በረጅም የታሪክ ጉዞዋ ሕዝቦቿን በማስተሳሰር የወል ትርክት መገንባት የሚያስችሉ በርካታ አጋጣሚዎችን ያስተናገደች ሀገር ናት። ለዚህም ከሩቁ የዓድዋ ድልን፣ ከቅርቡ ደግሞ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን መጥቀስ ይቻላል። እነዚህን ታሪካዊ አጋጣሚዎችም ለጋራ የወል ትርክት ግንባታ በመጠቀም ለዛሬ ብሎም ለነገ ሀገራዊ ራዕይ ስኬትና አንድነት አይተኬ ሚና አላቸው። ለዚህም ነው የኢትዮጵያን የጋራ ታሪክና እሴቶች ወደ የጋራ የወደፊት ራዕይ ማሸጋገር፣ ብዝሃነትን እያከበሩ አንድነትን ማጠናከር የወል ትርክት ዋነኛ እሳቤ መሆኑን የሚያስረዱት አማካሪ ሚኒስትሩ። ዓድዋ የነጻነት የጋራ ትርክት፤ ሕዳሴ ደግሞ የልማትና የራስ መተማመን የጋራ ትርክት ውጤት ሆኗል። ይህም የአንዱ ትውልድ ቅርስ የነጻነት እሴት ሲያስተላልፍ፣ ሌላው ደግሞ የዛሬውን ትውልድ በጋራ ራዕይ በማሰባሰብ የነገን የዕድገትና ብልፅግና ምኞት ተልሟል። የመደመር እሳቤም በእኛነት መርህ ላይ ተመሥርቶ ብዝሃነትን እንደ ስጋት ሳይሆን እንደ የጋራ ብልፅግና አቅም በመመልከት፣ የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የማዕዘን ድንጋይ አድርጎ እየሰራበት ነው። በዚህም የዓድዋ ድል ይህንን ታሪክ ያስተማረን ሲሆን፣ የሕዳሴ ግድብ ደግሞ በዘመናችን በተግባር የተገለጠ የአሰባሳቢ ትርክት ግንባታ የወል እውነት ማዕከልነትን ቀርጿል።
በጎነት የሰብዓዊ ክብር መሠረት፤ የመደመር መንግሥት የሰው ተኮር ልማት የተስፋ አድማስ
Sep 11, 2026 567
በጎነት ከኢትዮጵያውያን የዕለት ተዕለት ኑሮና እንቅስቃሴ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ፣ ከራስ ቀንሶ ለሌሎች መድረስ የሚገለጽበት ከፍ ያለ ሰብዓዊ እሴት ነው። በጎነት የግለሰብን ችግር ብቻ የሚያቃልል ተግባር አይደለም። የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክፍተቶችን በመሙላት አብሮነትን፣ መተሳሰብንና የጋራ ኃላፊነትን የሚያጠናክር የማህበራዊ ኃላፊነት ውልም ነው። ''ሃምሳ ሎሚ ለሃምሳ ሰው ጌጡ፤ ለአንድ ሰው ሸክሙ” እንዲል የሀገር ብሂል ሰዎች በአንድነት ቆመው ለአንድ መልካም ዓላማ ከተባበሩ ለመፍታት የማይቻል ችግር እንደሌለ በተግባር የሚያሳዩ ብዙ አብነቶች አሉ። በተለይም በሰው ተኮር ልማትና በበጎ ፈቃድ የሚከናወኑ የቤት ግንባታና እድሳት ሥራዎች ችግርን ከመቅረፍ ባለፈ የሰዎችን ሰብዓዊ ክብር የሚመልሱ የተስፋ ምንጭ ተግባራት ሆነዋል።   ባለፉት ዓመታት በሀገር አቀፍም ሆነ በአዲስ አበባ በበጋና ክረምት ሰው ተኮር የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሮች በርካታ ዜጎችን ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉስቁልና ወደ ልዕልና እንዲሸጋገሩ አስችሏል። ከእነዚህ የሰው ተኮር ተግባራት ተጠቃሚ ከሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች መካከል በመኖሪያ ቤት ችግር ምክንያት ኑሯቸው በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የነበሩ ነዋሪዎች ይገኙበታል። ቤት ለአንድ ሰው የመኖሪያ ቦታ ብቻ አይደለም። ይልቁንም የዜጎችን የደህንነት፣ የክብር፣ የመረጋጋትና ዘላቂ የተስፋ ወጋገን የሚያቆራኝ መሰረታዊ ጉዳይ ነው። ስለዚህ ለአንድ ቤተሰብ የሚገነባ ወይም የሚታደስ ቤት ከግንባታ ዕቃና ከግድግዳ በላይ ትርጉም አለው፤ የተሰበረ ተስፋን ይጠግናል፣ የተረሳ ክብርን ይመልሳል፣ ለነገም አዲስ እድል ይከፍታል። በአዲስ አበባ በበጎ ፈቃደኞች፣ በባለሀብቶችና በመንግሥት የጋራ ጥረት ቤት ተገንብቶላቸው እፎይታን ያገኙ ነፍሶችም በርካቶች ናቸው።   ወይዘሮ መስከረም ሰለሞን እንደሚሉት፤ ከዓመታት በፊት ከሁለት ልጆቻቸው ጋር ፒያሳ አካባቢ ለሰው ልጅ ክብርን በማይመጥን ጎስቋላ ቤት ውስጥ ሕይወትን ይመሩ ነበር። በተለይም ክረምት በመጣ ቁጥር የጎርፍና የዝናብ ፍሳሽ አደጋ በከፍተኛ ጭንቀት እንዲያሳልፉ ያስገድዳቸው እንደነበር አስታውሰዋል። በሳር ቤት አካባቢ በተሰራላቸው ዘመናዊ የመኖሪያ መንደር የተሰጣቸው የመኖሪያ ቤት አዲስ የሕይወት ተስፋን እንዳጎናጸፋቸው አስረድተዋል። ይህንም ለመኖር ከማይመች ቦታ ወጥቼ ወደ አማረ ቤት በመግባቴ እንደገና የመወለድ ያህል ታላቅ ደስታ ተሰምቶኛል ሲሉ ገልጸዋል። እንደ ወይዘሮ መስከረም ታሪክ ሁሉ የሌሎች ነዋሪዎች የቤት ግንባታና ዕድሳት ሥራዎች ተሞክሮ የሚያሳየው የቁሳዊ እፎይታ ብቻ ሳይሆኑ ሰብዓዊ ክብርን የሚያጎናጽፉ የተስፋ ውጤቶች መሆናቸውን ነው።   በአንድ ወቅት ከፎቅ ላይ ባጋጠማት የመውደቅ አደጋ ሳቢያ የአካል ጉዳት ያጋጠማት ታሪክ ሙሉጌታ፤ በአዲስ አበባ በኪራይና በመንግሥት ቤት ከቤተሰቧ ጋር ሕይወትን ስትገፋ እንደነበር ገልጻለች። የአካል ጉዳተኛ ከሆነች በኋላ ቀደም ሲል ትኖርበት የነበረው ቤትና አካባቢ ከቦታ ቦታ እንደልብ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ እንደነበር በማስታወስ፤ ከቤተሰቧ ጋር ይኖሩበት ከነበረው ባምቢስ አካባቢ ወደ ሳር ቤት አካባቢ የመኖሪያ ቤት ማግኘቷ በሕይወት ዘመን ያገኘሁት ትልቅ የተስፋ ስጦታዬ ነው ብላለች። ቤቱ እንደልብ መንቀሳቀስ የሚያስችል፣ መሠረታዊ የመኖሪያነት መስፈርቶች የተሟላላት መሆኑ ሕይወቴን በትልቅ እፎይታ እንድመራ አስችሎኛል ስትል ተናግራለች። በሰው ተኮር ፕሮጀክት የሚገነቡ ቤቶች የሚያመጡት ለውጥ ለአካል ጉዳተኞች ብቻ የሚወሰን አይደለም። በቤት ውስጥ ልጆች፣ አረጋውያን፣ የሀገር ባለውለታዎችና መላ ቤተሰብ እንዲሁም የተሻለ ኑሮን ለመፍጠር የሚታገሉ እናቶችና አባቶችም የዚህ ተግባር ተጠቃሚዎች ናቸው። በዚህም በጎነት የአንድን ሰው ዛሬ ከማሻሻል ባለፈ የአንድ ቤተሰብን ነገ የሚቀርጽ ኃይል መሆኑን ያሳያል።   ወይዘሮ ጽጌሬዳ ጎበና ፤ ለረጅም ዓመታት ፒያሳ አካባቢ ለመኖር ምቹ ባልሆነ ቤትና ሰፈር ከአንድ ልጃቸው ጋር ይኖሩ ነበር። በፒያሳ አካባቢ የሕይወት ቆይታ ዘመናቸውም ልዩ ድጋፍ የምትሻው ልጃቸው እንደልቧ መንቀሳቀስ የማትችልበትን በርካታ የሰቆቃ ጊዜያት እንዳሳለፈች አስታውሰዋል። በዚህ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ እያሉ በሳር ቤት አካባቢ አዲስ ቤት ማግኘታቸው እንደገና የመወለድ ያህል ትልቅ እፎይታን እንደቸራቸው ገልጸዋል። የተሰጣቸው ቤት ለልጃቸው እንቅስቃሴ ምቹ ከመሆኑ ባለፈ ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤን እንዲከተሉ ያስቻለ ታላቅ የሕይወት ብስራት መሆኑን ገልጸዋል። እነዚህ ታሪኮች የሚያስረዱት አንድ ቤት ሲታደስ ግድግዳና ጣሪያ ብቻ አለመሆኑን ነው። ከቤቱ ጋር የነዋሪው ተስፋ፣ የቤተሰቡ መረጋጋትና የሰው ልጅ ክብርም አብሮ ይታደሳል። በዚህም በጎነት የችግር መፍቻ ብቻ ሳይሆን ከጊዜ ጊዜ የተስፋ ማስፈንጠሪያና ሰብዓዊ ክብር ማጎናጸፊያ ተግባር እየሆነ መጥቷል።   በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቤታቸው ከታደሰላቸው መካከል ታየሁ መኮንን እንደሚሉት፤ ቀደም ሲል ይኖሩበት የነበረው ቤት 'ቤት ነው ለማለት እንኳን አያስደፍርም' ነበር። ዛሬ ግን ታሪካቸው ተቀይሯል። በበጎ ፈቃደኞች አማካኝነት የመኖሪያ ቤት ችግራቸው ተቀርፎ፣ 'ቤቴ በመታደሱ ያለ ሀሳብ ጎኔን ማሳረፍ ችያለሁ' ሲሉም ወይዘሮ ታየሁ ገልጸዋል። ይህ አንድ ነዋሪ ያገኘው የቤት ለውጥ ብቻ አይደለም። ከዓመታት የጭንቀት ኑሮ ወደ መረጋጋት የተሸጋገረ ሕይወት ነው። ከስጋት ወደ እፎይታ፣ ከተስፋ መቁረጥ ወደ ተስፋ የተደረገ ጉዞ ነው። ለበርካታ ዓመታት በማይመች ቤት ኑሮ ሲገፉ እንደቆዩ የገለጹት ወይዘሮ ዘውዲቱ ገብረማርያም ደግሞ፤ አሁን ላይ ቤታቸው በመታደሱ ደስ ብሏቸው የሚኖሩበትን ዕድል እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።   በሰው ተኮር የልማት መርሃ ግብር አቅመ ደካማ ወገኖችን ለመደገፍ የሚከናወኑ ተግባራትም የበርካቶችን ተስፋ የሚያለመልም አስደናቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። እነዚህ የነዋሪዎች ምስክርነቶች በጎነት በተግባር ሲገለጽ የሰውን ክብር እንደሚያጎናጽፍ፣ የተሰበረ ተስፋን እንደሚያድስና ለነገ የሚያስብ ሕይወትን እንደሚፈጥር ያረጋግጣሉ። በተለይም እናቶች፣ አረጋውያን፣ አቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎች የሚያገኙት ድጋፍ በቁሳዊ እርዳታ ብቻ የሚመዘን ሳይሆን 'እናንተም የዚህ ሀገር ክብር ናችሁ' የሚልን ሰብዓዊ መልዕክትን ያስተላልፋል። በዚህ ረገድ የመደመር መንግሥት ሰው ተኮር ልማትን እንደ የልማት ፖሊሲ አቅጣጫ በመያዝ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክፍተቶች በመሙላት ተስፋን የሚያለመልሙ ተግባራትን እያጠናከረ ይገኛል። የቤት ግንባታና ዕድሳት፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችና ሌሎች ሰው ተኮር መርሃ ግብሮችም ይህንኑ አቅጣጫ በተግባር ከሚያሳዩ ተጨባጭ ለውጦች መካከል ይጠቀሳሉ። አስተያየት ሰጪዎቹ ዛሬ ላይ ውብና ጽዱ በሆነ ቤት የሚኖሩበት ዕድል የተፈጠረው መንግሥት፣ ባለሀብቶችና ሌሎች በጎ ፈቃደኞች ባከናወኑት መልካም ተግባር በመሆኑ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በአዲስ አበባ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት አረጋውያንን፣ አቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎችን አመቺ መጠለያ እንዲያገኙ ለማድረግ የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በእርግጥም የበጎነት ዋጋው በሚሰጠው የቁሳቁስ መጠን ብቻ አይለካም። በሰው ልብ ውስጥ በሚፈጥረው ተስፋና በሕይወት ላይ በሚያመጣው ለውጥ ይመዘናል። የተሰራው ቤት ለአንዲት እናት የእፎይታ ምንጭ፣ ለአንድ አረጋዊ የክብር መገኛ፣ ለአካል ጉዳተኛ ደግሞ በራስ መተማመንና ነፃነት መገለጫ ይሆናሉ።   ይህም ሰው ተኮር ልማት ማለት ትልልቅ ፕሮጀክቶችን መገንባት ብቻ ሳይሆን፣ የአንድ ዜጋን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል፣ የአንድ ቤተሰብን ተስፋ ማደስና የአንድን ሰው ክብር ማስመለስ ጭምር መሆኑን ያሳያል። በጎነት ከአንድ ሰው ወደ ሌላው የሚሸጋገር ቀላል የመልካም ተግባር መገለጫ ቢመስልም በጋራ ሲተገበር ማኅበረሰብን የመለወጥ ታላቅ ኃይል አለው። የእነዚህ ነዋሪዎች ታሪክም ይህንኑ ያረጋግጣል። ከተስፋ መቁረጥ ወደ ተስፋ፣ ከስጋት ወደ እፎይታ፣ ከአስቸጋሪ ኑሮ ወደ የተሻለ ኑሮ የተሸጋገሩ ሕይወቶችን ያሳያል። ስለሆነም በጎነትን እንደ የአንድ ጊዜ ዘመቻ ሳይሆን እንደ የማኅበረሰብ የጋራ እሴት ማጠናከር፣ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን መደገፍና ሰው ተኮር ልማትን ማስቀጠል የጋራ ኃላፊነት ነው። ዛሬ የተሰራ ቤት ከግድግዳ በላይ ነው። የነገ ተስፋ መሰረት ነው። ዛሬ የተዘረጋ የበጎነት እጅም ከአንድ ሰው የሚተርፍ ለብዙዎች የሚደርስ የሰብዓዊነት ብርሃን ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም