ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የግብርናና የምግብ ሥርዓትን ማጠናከር ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት ወሳኝ ነው
Sep 9, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦የግብርናና የምግብ ሥርዓትን ማጠናከር አፍሪካ የአየር ንብረት ጫናን በመቋቋም ዘላቂ ልማቷን እንድታሳድግ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ ከጳጉሜን 2 እስከ 4 ቀን ሲካሄድ የቆየው አህጉራዊ ጉባኤ ፍጻሜውን አግኝቷል። በጉባኤው ወቅት በአፍሪካ የግብርናና የምግብ ሥርዓትን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በማጣጣም የሕዝቦችን የምግብ ዋስትና እና የኑሮ ጽናት ለማሻሻል የሚያስችሉ ዋና ዋና አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በዚሁ መድረክ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን የአህጉሪቱን የግብርናና የምግብ አጀንዳ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ውይይቶች የበለጠ ማስገንዘብና ውሳኔዎችንም ወደ ተግባር ማሸጋገር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ህብረት (Alliance for Food Sovereignty in Africa - AFSA) አስተባባሪ ዶክተር ሚሊዮን በላይ እንደገለጹት፤ አፍሪካ በግብርናና በምግብ ሥርዓት ያላትን የራሷን ልምድና መፍትሔ በማጠናከር በአህጉርና በዓለም አቀፍ መድረኮች የራሷን አጀንዳ በተግባር ማስፈጸም ይገባታል። አህጉሪቱ በዘርፉ ያላትን መልካም ተሞክሮ የበለጠ ማጉላት እንዳለባት ጠቁመው ለተቋቋሚ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አግሮ-ኢኮሎጂን ማስፋፋት፣ የገበሬዎችን የዘር ሀብት መጠበቅና የገበሬዎችን ተሞክሮ ከሳይንስ ጋር በማጣመር የተሻለ የግብርና ልማት ማምጣት እንደሚገባ አስረድተዋል። በተጨማሪም የአፈርና የውሃ ሀብትን በአግባቡ መጠቀም፣ የአካባቢ የምግብ ገበያዎችን ማጠናከርና አፍሪካ የምግብ ፍላጎቷን በተቻለ መጠን በራሷ ምርትና ሀብት በመሸፈን የምግብ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ እንደሚገባት ገልጸዋል። የምግብ ሥርዓቱ ቀጥተኛ ተዋናዮች ሀሳባቸው በውሳኔዎች ውስጥ እንዲንጸባረቅ የሚያስችል ተጨባጭ ተሳትፎ ሊኖራቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ በዘር ሀብት ጥበቃ፣ በአግሮ-ኢኮሎጂና በምግብ ሉዓላዊነት ያላትን ልምድ በማጠናከር ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ ማካፈል እንደምትችል ጠቁመዋል፡፡ የአርሶ አደሮችን የዘር ሀብት መጠበቅና አሀጉራዊ ተሞክሮዎችን ከሳይንሳዊ እውቀት ጋር በማጣመር የተሻለ የግብርና ልማት ለማስመዝገብ መስራት እንደሚገባ አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ጥንካሬ በብዝሃነትና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት ላይ የፀና ነው
Sep 9, 2026 131
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጥንካሬ በብዝሃነትና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት ላይ የፀና መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ፡፡ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጳጉሜን 4 "የሕብር ቀን"ን በማስመልከት ልዩ የኪነ-ጥበብ ምሽት አከናውኗል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ ሚኒስትሮች፣ የሥራ ኃላፊዎች፣ ተጋባዥ እንግዶችና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል፡፡ የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ ህልውናና ጥንካሬ በብዝሃነት፣ በህብረ-ብሔራዊ አንድነት ላይ የሚጸና መሆኑን አስረድተዋል። የቀደሙ አባቶችና እናቶች አብሮነታቸውን አጎልብተው ያቆዩልንን ሀገር፣ እኛም በአንድነት ተጠናክረን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ ቃላችንን የምናድስበት ወቅት ነው ብለዋል። በጋራ ህልውናዋን ጠብቀንና ከፍ አድርገን ለትውልድ ማስተላለፍ የሁላችንም ሃላፊነት መሆኑን አብራርተዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፀጋዬ ማሞ በበኩላቸው፤ ህብር የብዙ ልዩነቶች ድምር ውጤትና የአንድነት ጥንካሬ በመሆኑ፣ አዲሱን ዓመት ስንቀበል የመደመር፣ የመደጋገፍና የፍቅር መንፈስን በማንገብ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ የባህሎች፣ የቋንቋዎችና የእምነቶች መኖሪያ በመሆኗ ይህ ህብረ-ብሔራዊነት የታላቅነትና የውበት ምስጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን በርካታ ፈተናዎች ማለፍና ተሻጋሪ ዕቅዶችን ማሳካት የተቻለውም ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው በጋራ ዓላማ በመቆም ብቻ እንደሆነ አስረድተዋል።
በአዲሱ ዓመት የማዕድ ማጋራትና የመደጋገፍ ባህልን ይበልጥ ማጎልበት ወሳኝ ነው
Sep 9, 2026 101
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲሱ ዓመት የማዕድ ማጋራትና የመደጋገፍ ባህልን ይበልጥ ማጎልበት እንደሚገባ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ጌታቸው በዳኔ ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የዘመን መለወጫ በዓልንና የሕብር ቀን ምክንያት በማድረግ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የሴቶች ማረፍያና ልማት ማኅበር ለሚገኙ ሴቶች ማዕድ አጋርቷል። በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትር አማካሪ ጌታቸው በዳኔ በዚሁ ወቅት በሕብር ቀን ሚኒስቴሩ ለስርዓተ ጾታ እኩልነት እና ለማህበራዊ ደህንነት መረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ለሀገር እድገት፣ ሰላምና ማህበራዊ መረጋጋት ከሚሰጡ ቅድሚያዎች መካከል አንዱ የሴቶችን መብት ማስከበር እንደሆነ አመልክተዋል። የሴቶችን መብት ለማስጠበቅ ከሚደረገው ጥረት ጎን ለጎን፣ በተለያዩ ምክንያቶች ለጥቃትና ለችግር የተጋለጡ ሴቶችን የማህበራዊና ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በዘላቂነት መልሶ ለማቋቋም የሚያግዙ ተግባራትን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እያከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ በዛሬው ዕለትም በተለያዩ ምክንያቶች ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ማረፊያና ልማት ማኅበር የአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በዓይነትና በገንዘብ ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡ የሕብር ቀን አብሮነትንና ማህበራዊ ትስስርን ይበልጥ የሚጠናከርበትና የመደጋገፍ እሴትን በተግባር የሚገለጥበት መሆኑን ተናግረዋል። የዛሬው ማዕድ ማጋራትም እርስ በእርስ የመረዳዳት ባህል የሚያሳይ፣ አዲሱን ዓመት በተስፋ፣ በደስታ እና በሙሉ ስነ-ልቦናዊ ዝግጅት ለመቀበል እንዲያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ የተደረገው የበጎ አድራጎት ተግባርም ይህንን ታሪካዊ እሴት በመጠበቅ ለሚመጣው ትውልድ ለማስተላለፍ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። የሴቶች ማረፍያና ልማት ማኅበር ዋና ዳይሬክተርና መስራች ማርያ ሙኒር በበኩላቸው፤ በተደረገው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸው፣ ለዚህም በተጠቃሚዎች ስም ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዕዳ ተላቆ ወደ ውጤታማ የትርፋማነት ምዕራፍ ተሸጋግሯል - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ
Sep 9, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከነበረበት ዕዳ ተላቆ ወደ የትርፋማነት ምዕራፍ መሸጋገሩን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞቹ በተገኙበት የዘንድሮውን የ2018 በጀት ዓመት "ንጹህ ኢነርጂ ለተሻለ ሕይወት" በሚል መሪ ሐሳብ የተቋም ቀኑን አክብሯል። ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በዚህ ወቅት፤ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢትዮጵያን የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል የማድረግ ራዕይ የሚያሳካ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በ2018 በጀት ዓመት በርካታ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን፣ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በመሥራት ተቋማዊ የመፈጸም አቅምን ማላቅ መቻሉን አስታውቀዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የአሰላና የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ ኃይል የማመንጨት አቅምን ወደ 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት በማሳደግ የ23 በመቶ ዕድገት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ተናግረዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ጠቅላላ የኃይል ምርት አቅም 35 ሺህ 671 ጊጋ ዋት በሰዓት በማድረስ የ124 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘት እንደተቻለ አስረድተዋል። ከኃይል ሽያጭና ዳታ ማይኒንግ 475 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ መገኘቱም የተቋሙን የገቢ አቅም ከባለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ64 በመቶ ዕድገት እንዲመዘገብ አስችሏል ብለዋል። በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ 39 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ በማስመዝገብ ተቋሙ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዕዳ ወደ ትርፋማነት የተሸጋገረበትን ስኬታማ ዘመን እንዳሳለፈ ጠቅሰዋል። በዚህም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከነበረበት ዕዳ ተላቆ ወደ ውጤታማ የትርፋማነት ምዕራፍ መሸጋገሩን አብስረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ላስመዘገበው ስኬትም የተቋሙ አመራር፣ ሠራተኞችና ባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ መሆኑን በማንሣት ለዚህ ሁሉንም አመስግነዋል። ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የሁሉም ዜጎች ኩራትና አሻራ ያረፈበት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ በይፋ የተመረቀበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑንም አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ቀንም የሕዳሴን ታሪካዊ ፍጻሜ በመዘከር የላቀ አፈጻጸም ለነበራቸው አመራርና ሠራተኞች ዕውቅና ለመስጠት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በየዓመቱ ጳጉሜን 4 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ቀን ሆኖ እንደሚከበር አስታውቀዋል።
የዲጂታል አብዮት ለነገዋ ኢትዮጵያ
Sep 9, 2026 108
በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ የዛሬን ፈታኝ ሁኔታዎች ከመቅረፍ ባለፈ፣ ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር በፍጥነት እያሸጋገራት ይገኛል። የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታዎች እና የተቋማት ማጠናከሪያ ስራዎች ለዚሁ አገራዊ የነገ ትራንስፎርሜሽን በምሳሌነት የሚጠቀሱ ዋና ዋና እርምጃዎች ናቸው። መንግስት የዲጂታል ዘርፉን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሶሶ በማድረግ የነደፈውን "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ስትራቴጂ በስኬት ማጠናቀቁ፣ 2030 ዲጂታል ስትራቴጂን መጀመሩ ሀገሪቱን በቴክኖሎጂው ዘርፍ ወደ አዲስ የወደፊት ምዕራፍ እንድትገባ ያስቻለ መሰረታዊ ለውጥ አምጥቷል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ፣ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም መዘመን ለኢንተርኔት ተደራሽነት መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። በተለይም የ5G ቴክኖሎጂ አገልግሎት በስፋት መጀመሩ ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ በቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትና በመሰረተ ልማት ዝግጁነት ቀዳሚ ያደረጋት ሲሆን፣ ይህም ለነገው ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እና ለቀጣይ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቱ መዘመን በፋይናንስ ዘርፉ ላይ አብዮታዊ ለውጥ በማምጣት የነገዋን ስማርት ኢኮኖሚ መደላደል ጥሏል። እንደ ቴሌብር ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ ለአካታች ዲጂታል ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም ሆነዋል። ይህ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ምህዳር መስፋፋት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የዲጂታል ክፍያዎችን እንዲቀበሉና የፋይናንስ ተደራሽነታቸው እንዲያድግ ያስቻለ ሲሆን፣ መደበኛ ያልሆነውን የግብይት ስርዓት ወደ ዘመናዊና ግልጽ የነገ ዲጂታል ስርዓት የመቀየር ሂደቱን አፋጥኖታል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የኢትዮጵያ ሰውሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም የሀገሪቱን ታላቅ የነገ ራዕይ ለዓለም አሳይቷል። ኢንስቲትዩቱ በጤናው ዘርፍ የካንሰርና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ የሚያውቁ የኤአይ ውጤቶችን በማበልጸግ ህይወትን የማዳን ስራ እያከናወነ ይገኛል። በተመሳሳይ በግብርናው ዘርፍ የአፈር ለምነትንና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም ለነገዋ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥና ለምርታማነት ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ የለውጡ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል አለም ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱ በማድረግ ለነገው ትውልድ የባህል እና የእውቀት መተላለፊያ ምቹ መንገድ ፈጥሯል። ከዚሁ ጎን ለጎን የ"ፋይዳ" (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት የዜጎችን መረጃ በማደራጀት ለነገው ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ አስተማማኝ የመረጃ መሰረት ጥሏል። ይህም ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ቀልጣፋ አሰራርን ፈጥሯል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የነገዋን አሰራር ዛሬ ማሳያ ሲሆን፣ የሳይንስ ሙዚየም ደግሞ የነገዎቹን ፈጣሪዎች አቅም የሚያበለጽግ ማዕከል ሆኗል። በተጨማሪም በዲጂታል ክህሎት ግንባታ ረገድ ለወጣቶችና ለባለሙያዎች የሚሰጡ የስልጠና ፕሮግራሞች በስፋት እየተካሄዱ ይገኛሉ። ይህም ኢትዮጵያ በነገው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መድረክ ብቁ እና ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ኃይል እንድታፈራ ዘላቂ መሰረት እየጣለ ነው።
ፖለቲካ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአፍሪካ ሕብረት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
Sep 9, 2026 234
አዲስ አበባ ፤ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ24ኛ የአፍሪካ ሕብረት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጀምሮ እስከ አሁኑ የአፍሪካ ሕብረት ድረስ በአህጉሪቱ ጉዞ ውስጥ ጽኑ ድምፅ ሆና የቆየችና አሁንም ያለች ሀገር ነች፤ አዲስ አበባም የአህጉራዊ ሕብረታችን መኖሪያ ሆና ታገለግላለች ብለዋል።
ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ዕድገት መትጋት ይገባል
Sep 9, 2026 211
ባህር ዳር፤ ጳጉሜ 4/2018(ኢዜአ)፦ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ዕድገት መትጋት ይገባናል ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ገለጹ። በክልሉ የሚገኙ የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት የህብር ቀንን በባህር ዳር ከተማ በድምቀት እያከበሩ ነው። የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር ) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የህብር ቀን የሀገሪቱን ብዝሃነት፣ አብሮነትና አንድነት የምናስብበት ታላቅ ዕለት ነው። ዕለቱን ስናስብ የጋራ ትርክትን በማጎልበት ለአገር እድገትና ብልጽግና በቅንጅት የመቆም ባህልን የምናጎለብትበት ነው ሲሉም አመልክተዋል። "በጋራ ስንቆም እንበረታለን" ያሉት አስተባባሪዋ፣ አብሮነታችን ለጠላት እሳት፣ ለወዳጅ ደግሞ የብረት አጥር ለመሆን የሚያስችል ነው ብለዋል። አክለውም ዕለቱን ስናስብ በማዳመጥ፣ በመከባበርና በመተባበር ለህብረ ብሔራዊ አንድነት መጠናከር የድርሻችንን በመወጣት መሆን አለበት ነው ያሉት። በአዲሱ ዓመትም የተግባር ሰው በመሆን ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባም አንስተዋል። የብሔር፣ የቋንቋና የሃይማኖት ልዩነቶች ሳይገድቡ ሕብረ ብሔራዊነትን ለሀገር ግንባታ በመጠቀም መስራት እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ በበኩላቸው፤ ዕለቱ የብዝሃነት መገለጫና የተሰናሰለ አንድነታችን ማሳያ ነው ብለዋል። የጳጉሜን ቀናትን ስናከብር ያለፈውን የምንገመግምበት፣ አብሮነትና የጋራ ጽናት በህብር የምናሳይበት ለቀጣይ ሥራ መነሳሳትን የፈጠረ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በተጨማሪም ዕለቱ ማዕድ በማጋራት፣ ደም በመለገስ፣ ነፃ ህክምና በመስጠትና ለልጆች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በማበርከት መከበሩ ለተተኪው ትውልድ መልካም መሰረት የሚጥል መሆኑን አስረድተዋል።
ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር አስተሳሳሪ የወል ትርክት ግንባታ ውጤት እያስመዘገበ ነው
Sep 9, 2026 266
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ ብዝሃነትና ህብረ ብሔራዊነት መሠረት ያደረገ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር አስተሳሳሪ የወል ትርክት የመገንባት ተግባር ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን የሕገ መንግሥትና ፌዴራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኃይለኢየሱስ ታዬ (ዶ/ር) ገለጹ። ህብረ ብሔራዊነትን ማጎልበት ሀገራዊ አንድነትን፣ ሰላምንና የልማት ዕድገትን ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑንም ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት። ኢትዮጵያ በህብረ ብሔራዊነት የደመቀች ለሀገራዊ እሴቶች እና ግቦች የሚተጉ እንዲሁም በጋራ እጣ ፈንታ የተሳሰሩ ህዝቦች ያሏት ሀገር ናት። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት ኃይለኢየሱስ ታዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያን ብዝሃነት እና ህብረ ብሔራዊነት ለወል ትርክት ግንባታ በማዋል አስተሳሳሪ ትርክት ከመገንባት አኳያ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊ ብዝሃነት ያላት ሀገር መሆኗን ጠቁመው፤ ይህንን ብዝሃነት በተገቢው መንገድ ማስተናገድ የጋራ ሀገራዊ ማንነትን ለመገንባት መሠረት መሆኑንም አክለዋል። በዚህም ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊነት በተገቢው በመመራቱ ለሀገር ጥንካሬ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ህብረ ብሔራዊነት አንዱ የሀገራዊ ትርክት ግንባታ ማዕከል መሆኑን ገልጸው፤ ሁሉም ቋንቋዎች፣ ባህሎችና ማንነቶች ለሀገር ግንባታ ወሳኝ መሆናቸውን ተናግረዋል። አሰባሳቢ ትርክት በሀገራዊ ስኬቶች፣ በልማትና በሀገሪቷ ህብረ ብሔራዊነት ላይ ሊመሠረት እንደሚችልም ነው ጨምረው የገለጹት። የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከባበር የኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊነት ጎልቶ የሚታይበት ብቻ ሳይሆን ሀገራዊ አንድነት የሚጠናከርበት መሆኑን ጠቁመዋል። ማዕከሉ የኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ግንዛቤ በመፍጠር በኩል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። የፌዴራል ሥርዓቱ የሚጠይቀው ዕውቀት፣ ክህሎትና አስተሳሰብ እንዲጎለብትም በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ፌዴራሊዝም በብዝሃነት የተገነባች ሀገር ውስጥ የተለያዩ ማንነቶችን አሳታፊ በሆነ መንገድ ለማስተናገድና የጋራ ሀገር ግንባታን ለማጠናከር ጠቃሚ ሥርዓት መሆኑንም ተናግረዋል። አክለውም የፌዴራሊዝም ሥርዓቱ የተለያዩ አካባቢዎች ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩና አካባቢያቸውን እንዲያለሙ ዕድል በመስጠት የልማት አቅሞችንና ፍላጎቶችን ለማስታረቅ አግዟል ብለዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ በብዝሃነት ውስጥ አብሮ የመኖር ልምድ ማካበቱንና ይህንን የአብሮነት እሴት ወደ ሀገራዊ የጋራ እሴትነት ለማሸጋገር በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቁመው፤ ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ስለሆነም ህብረ ብሔራዊነትን ከፌዴራሊዝም እና ከዴሞክራሲ እንዲሁም ከልማትና ከሀገራዊ እሴቶች ጋር በማጣመር የጋራ ሀገራዊ ማንነትና አንድነትን ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
አዲሱ ዓመት ተጨማሪ ዲፕሎማሲያዊ ድሎችን ለማስመዝገብ የበለጠ የምንሰራበት ነው
Sep 9, 2026 205
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦አዲሱ ዓመት ባለፈው ዓመት ከተመዘገቡት ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች በመነሳት ተጨማሪ ድሎችን ለማስመዝገብ፣ አዲስ ዕይታን ለመላበስና አዲስ ክህሎትን ለማዳበር ትልቅ አጋጣሚ የሚፈጥር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳም ተስፋዬ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ጳጉሜን 4 የኅብር ቀንን ‘’ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ" በሚል መሪ ሐሳብ በጋራ አክብረዋል፡፡ በበዓሉ ሥነ-ሥርዓት ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም የጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች ተገኝተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳም ተስፋዬ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፤ በተጠናቀቀው ዓመት በመሠረተ ልማት፣ በኢኮኖሚ፣ በአካባቢ ጥበቃና በዲፕሎማሲ ዘርፎችና በሌሎችም ከፍተኛ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። የጳጉሜን ቀናት እመርታን፣ ማንሠራራትን፣ ጽናትን፣ ኅብርንና ነገን በማሰብ ስኬቶችን የምንቆጥርበት እንዲሁም ለአዲሱ ዓመት አዲስ ራዕይ የምንሰንቅበት ወቅት ነው ሲሉም አብራርተዋል። የተመዘገቡትን የዲፕሎማሲ ስኬቶች መሠረት በማድረግ በአዲሱ ዓመት ለላቀ ውጤት እና ለተጨማሪ ድሎች በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።
ግብጽ ጊዜው ያለፈበትን አካሄድ በመተው በአባይ ወንዝ ላይ ያለውን አዲስ እውነታ መቀበል አለባት-ቲቦር ናጊ
Sep 9, 2026 267
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ግብጽ ጊዜው ያለፈበትንና ዘመኑን የማይመጥን አካሄድ ትታ በአባይ ወንዝ ላይ ያለውን አዲስ እውነታ መቀበል አለባት ሲሉ የቀድሞው የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቲቦር ናጊ ገለጹ። የቀድሞው የአሜሪካ ዲፕሎማት አባይን በተመለከቱ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ቆይታ ማድረጋቸውን በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል። ግብፅ አሁን ያለንበት ዘመን 19ኛው እና 20ኛው ክፍለ ዘመን ሳይሆን 2026 መሆኑን በውል ከተገነዘበች ከኢትዮጵያ ጋር አባይን በተመለከተ ሁለቱንም ወገኖች አሸናፊ የሚያደርግ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻል አፅንኦት ሰጥተው መናገራቸውን አመልክተዋል። ቲቦር ናጊ ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ጋር በቅርቡ በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን በውሃ ሃብቷ የመልማት መብት ግብጽ ልታከብር እንደሚገባ ገልጸዋል። የቀጣናው ፖለቲካዊ ገጽታ ከፍተኛ ለውጥ ማሳየቱን የገለጹት ቲቦር ናጊ፣ ግብፅ በአሁኑ ሰዓት አዲስ የኃይል ሚዛን መፈጠሩንና ኢትዮጵያም እጅጉን ማደጓን ልትገነዘብ እንደሚገባ አስምረውበታል። ግብፅ የድርድር አቀራረቧን ዳግም በመመርመርና አዲስ እና አዎንታዊ አመለካከት ይዛ ወደ ንግግር ጠረጴዛው ከተመለሰች ዘላቂና ፍትሃዊ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻልም ነው ያነሱት። የሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት የውሃ ሀብቶችን የመጠቀም መብት እውቅና መስጠት ላይ የተመሰረቱ ውይይቶች የጋራ መግባባት ሊፈጥሩ እንደሚችሉም ተናግረዋል። ቲቦር ናጊ የኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሃብት መጠቀም ራስ ወዳድነት ወይም በግብፅ ላይ የህልውና አደጋ ተደርጎ መታየት የለበትም ሲሉ አስገንዝበዋል። አገራት የራሳቸውን የተፈጥሮ ሃብት ይጠቀማሉ። ሁሉንም ነገር በእውነታው ላይ ቆመን እንመልከት ብለዋል። የቀድሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቲቦር ናጊ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት በተመለከተም ሀሳባቸውን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ፍትሃዊና ሕጋዊ ጥያቄ መሆኑን የገለጹት ቲቦር ናጊ፣ የጎረቤት ሀገራት የኢትዮጵያን ፍላጎቶች በሚገባ መረዳት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ትውልዱ በጀግኖች መስዋዕትነት የቆየችውን ሀገር ከነክብሯ የማጽናት አደራ አለበት
Sep 8, 2026 417
ዲላ፤ ጳጉሜን 3/2018 (ኢዜአ)፡-ጀግኖች ለሀገራቸው ዋጋ ከፍለው ያቆዩዋትን ኢትዮጵያ የዛሬው ትውልድ ከነክብሯ የማጽናት አደራ አለበት ሲሉ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገለጹ። ጳጉሜን-3 የጽናት ቀን በጌዴኦ ዞን እና በዲላ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል። የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘመናት ጸንታ የኖረችና በቅኝ ግዛት ያልተገዛች የጥቁር ህዝቦች ኩራት ናት። በውስጥና በውጭ ጠላቶች በየዘመናቱ ኢትዮጵያን ለመበታተንና ለማፍረስ የተደረገው ጥረት በቁርጥ ቀን ልጆቿ ጽናትና የደም ዋጋ ጭምር ማክሸፍ ተችሏል ብለዋል። ይሁንና ዛሬም ባንዳና ባዳ ሀገራችን ኢትዮጵያን ለማዳከም ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተባብረው እየሰሩ መሆኑን ያስታወሱት ዋና አስተዳዳሪው፣ በየዘመናቱ ጀግኖች ለሀገራቸው ዋጋ ከፍለው ያቆዩዋትን ኢትዮጵያ የዛሬው ትውልድም ከነክብሯ ማጽናት አደራ አለበት ብለዋል። በዚህም ትውልዱ በተለይ ወጣቱ የአካባቢውን ሰላም ከመጠበቅ ባለፈ ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት የሚያደርገውን ጥረት ማጠናከር አለበት ሲሉ አሳስበዋል። ጀግኖች አባቶች የደምና አጥንት ዋጋ ከፍለው ሉዓላዊነቷ የተከበረ ሀገር ለእኛ አስረክበውናል ያሉት ደግሞ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ናቸው። ዛሬ የጽናት ቀን ሲከበር ከአባቶቻችን መስዋዕትነትና ጽናት በመማር ከድህነት የተላቀቀች ሀገር ለመገንባት በየዘርፉ በሚደረገው ጥረት በንቃት በመሳተፍና በማገዝ መሆን አለበት ብለዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በተሰማራበት መስክ ለሀገሩ በጽናት በመቆም ሕብረ ብሔራዊ አንድነቷና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማሻገር የበኩሉን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአከባበሩ ላይ የተገኙት የዲላ ከተማ ነዋሪው አቶ አለማየሁ ጅግሶ በበኩላቸው፤ የጽናት ቀን ሲከበር ለህዝቦች ሰላምና ለሀገር ሉዓላዊነት መስዋዕትነት የከፈሉ ባለውለታዎችን በማሰብ መሆኑ ተገቢ ነው ብለዋል። ለከተማቸው ዘላቂ ሰላም ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ለማስቀጠል የበኩላቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።
የሀገርን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በጽናት እየተጋን ነው
Sep 8, 2026 338
ድሬዳዋ፤ ጳጉሜን 3/2018 (ኢዜአ)፡-የሀገርን ሉአላዊነት፤ ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በጽናት እየተጉ መሆናቸውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፀጥታ አባላት ገለጹ። በድሬዳዋ የሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፀጥታ አባላት የፅናት ቀንን በወታደራዊ ትርዒትና በሌሎች ስነ ስርአቶች አክብረዋል። በቀኑ አከባበር ላይ የተሳተፉት የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የጸጥታ አባላት ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የሀገርን ሉአላዊነትና ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከመቼውም ጊዜ በላይ በጽናት እየተጉ ነው። በዚህም ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት መካከል መቶ አለቃ ማማሩ ታዬ እንዳስታወቁት፤ሠራዊቱ አንድነቱንና ህዝባዊነቱን ጠብቆ የሀገርን ሉአላዊነት ለማፅናት ተጋድሎውን አጠናክሯል። ሠራዊቱ ከአባቶቹ የወረሰውን ጀግንነት በማስቀጠል የኢትዮጵያን ከፍታ ለማፅናት በቁርጠኝነት እየተጋ መሆኑን አስታውቀዋል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገርን ሉአላዊነት ከውጭና ከውስጥ ጠላቶች የመጠበቅ ተልዕኮውን በቁርጠኝነት እየተወጣ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አስር አለቃ ምህረትዓለም ባደለ ናቸው። የፅናት ቀን መከበሩ ሠራዊቱ ለሀገር መከበር ለከፈለው መስዋትነት እውቅናን በመስጠቱ ሰራዊቱ ግዳጁን በታላቅ ጀብድ ለመወጣት እንደሚያነሳሳው ጠቁመዋል። የፅናት ቀን ሰላምና ፀጥታ በአስተማማኝ መንገድ የመጠበቅን ተልዕኮ በላቀ ደረጃ ለመወጣት ቃላቸውን ያደሱበት መሆኑን ያነሱት ደግሞ የፌደራል ፖሊስ አባል ዋና ሳጅን ጠብቀው መርድ ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አባል ኮንስታብል ቅድስት ውብሸት በበኩላቸው፤ የፀጥታ መዋቅሮች ከህብረተሰቡ ጋር ትስስራቸውን በማጠናከር የነዋሪውን ሰላምና ፀጥታ በማረጋገጥ በላቀ ብቃት እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በእለቱ ሀገርን በማፅናት እና ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ ተግባራት ላይ አበርክቶ ላላቸው ተቋማት የተዘጋጁ ሽልማቶች ተበርክተዋል።
የሀገርን ሰላምና ልማት ቀጣይነትን የማረጋገጥ ተልዕኳችንን በጽናት እንወጣለን
Sep 8, 2026 349
ሀዋሳ፤ ጳጉሜን 3/2018 (ኢዜአ)፡-የሚቃጡ የጠላት ሴራዎችን በቅንጅት በማክሸፍ የሀገር ሰላምና ልማት ቀጣይነትን የማረጋገጥ ተልዕኳቸውን በጽናት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን የአገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌደራል ፖሊስ አመራሮች ገለጹ። ''በፅናት ችግርን እንሻገር፤ በአንድነት የተሻለች ሀገር እንገንባ'' በሚል መሪ ሀሳብ የ''ፅናት ቀን'' በሲዳማ ክልል ደረጃ በሀዋሳ ከተማ በተለያዩ መርሀ ግብሮች ተከብሯል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌደራል ፖሊስ አመራሮች የሀገር ሰላምና ልማት ቀጣይነት እንዲረጋገጥ ከውጭም ከውስጥም የሚቃጡ የጠላት ሴራዎችን በቅንጅት የማክሸፍ ተልዕኳቸውን በጽናት ለመወጣት ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል። የሀገርን ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የሠራዊት አባላት ሚናቸውን አጠናክረው እንደሚወጡም ተናግረዋል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት የደቡብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የጠቅላላ አገልግሎት መምሪያ ሃላፊ ኮሎኔል የሽዋስ ደምሴ እንደተናገሩት፤ የሠራዊት አባላት ለሀገር ሉአላዊነት መከበር በጽናት የሚከፍሉት የሕይወት ዋጋ መተኪያ የሌለው ነው። የሠራዊቱ አባላት የሀገር ዳር ድንበርና ሉአላዊነትን በማስጠበቅ ግዙፍ የልማት ግቦች እንዲሳኩ በጽናት ሲሰራ መቆየቱን አስታወሰዋል፡፡ በጽናት መቆም ለወታደር ብቻ የሚተው አይደለም ያሉት ኮሎኔል የሽዋስ፣ ሁሉም ለሀገር ሰላምና እድገት በጽናት በመቆም የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አለበት ብለዋል። በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የደቡብ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ መምሪያ የሰው ሀብት ሥራ አመራር ምክትል መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ሲሳይ ገላን በበኩላቸው፣ የሀገር ሰላምና ልማትን በዘላቂነት አጠናክሮ ለማስቀጠል ሠራዊቱ ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው ብለዋል ። በፀረ ሰላም ሀይሎች የሀገርና የህዝብ ሰላም እንዳይታወክ ለመከላከል የፌደራል ፖሊስ አባላት ሁልጊዜ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸው፣ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ እንዲፋጠን በየጊዜው የሚቃጡ የጠላት ሴራዎችን በቅንጅት የማክሸፍ ተልዕኮን በጽናት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ህዝቡ የልማት ተሳትፎውን እንዲያጠናክር የፖሊስ አባላት ሰላምን በዘላቂነት የማስጠበቅ ተልዕኳቸው ላይ አተኩረው እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የጽናት ቀንን ስናከብር ውስብስብ ፈተናዎች አልፋ በብልጽግና ጉዞ ላይ ያለችውን ኢትዮጵያ ልማቷን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለንን ጽናት በማረጋገጥ መሆን አለበት ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ ዳዊት ዳንጊሶ ናቸው። ጀግኖች አባቶች በከፈሉት መስዋዕትነት ነጻነቷ ተጠብቆ የቆየችውን ኢትዮጵያ ልማቷን በማፋጠን ለቀጣይ ትውልድ ያደገች ሀገር ለማስረከብ ሰላሟን በጋራ ልናጸና ይገባል ብለዋል። የተጀመሩ የልማትና የብልጽግና ግቦችን ከዳር ለማድረስ ፖሊስ ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በተናበበ መልኩ በጽናት የሚያደርገውን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክር የገለጹት ደግሞ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ተስፋዬ ዴቢሶ ናቸው።
ፖለቲካ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአፍሪካ ሕብረት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
Sep 9, 2026 234
አዲስ አበባ ፤ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ24ኛ የአፍሪካ ሕብረት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጀምሮ እስከ አሁኑ የአፍሪካ ሕብረት ድረስ በአህጉሪቱ ጉዞ ውስጥ ጽኑ ድምፅ ሆና የቆየችና አሁንም ያለች ሀገር ነች፤ አዲስ አበባም የአህጉራዊ ሕብረታችን መኖሪያ ሆና ታገለግላለች ብለዋል።
ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ዕድገት መትጋት ይገባል
Sep 9, 2026 211
ባህር ዳር፤ ጳጉሜ 4/2018(ኢዜአ)፦ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ዕድገት መትጋት ይገባናል ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ገለጹ። በክልሉ የሚገኙ የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት የህብር ቀንን በባህር ዳር ከተማ በድምቀት እያከበሩ ነው። የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር ) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የህብር ቀን የሀገሪቱን ብዝሃነት፣ አብሮነትና አንድነት የምናስብበት ታላቅ ዕለት ነው። ዕለቱን ስናስብ የጋራ ትርክትን በማጎልበት ለአገር እድገትና ብልጽግና በቅንጅት የመቆም ባህልን የምናጎለብትበት ነው ሲሉም አመልክተዋል። "በጋራ ስንቆም እንበረታለን" ያሉት አስተባባሪዋ፣ አብሮነታችን ለጠላት እሳት፣ ለወዳጅ ደግሞ የብረት አጥር ለመሆን የሚያስችል ነው ብለዋል። አክለውም ዕለቱን ስናስብ በማዳመጥ፣ በመከባበርና በመተባበር ለህብረ ብሔራዊ አንድነት መጠናከር የድርሻችንን በመወጣት መሆን አለበት ነው ያሉት። በአዲሱ ዓመትም የተግባር ሰው በመሆን ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባም አንስተዋል። የብሔር፣ የቋንቋና የሃይማኖት ልዩነቶች ሳይገድቡ ሕብረ ብሔራዊነትን ለሀገር ግንባታ በመጠቀም መስራት እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ በበኩላቸው፤ ዕለቱ የብዝሃነት መገለጫና የተሰናሰለ አንድነታችን ማሳያ ነው ብለዋል። የጳጉሜን ቀናትን ስናከብር ያለፈውን የምንገመግምበት፣ አብሮነትና የጋራ ጽናት በህብር የምናሳይበት ለቀጣይ ሥራ መነሳሳትን የፈጠረ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በተጨማሪም ዕለቱ ማዕድ በማጋራት፣ ደም በመለገስ፣ ነፃ ህክምና በመስጠትና ለልጆች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በማበርከት መከበሩ ለተተኪው ትውልድ መልካም መሰረት የሚጥል መሆኑን አስረድተዋል።
ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር አስተሳሳሪ የወል ትርክት ግንባታ ውጤት እያስመዘገበ ነው
Sep 9, 2026 266
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ ብዝሃነትና ህብረ ብሔራዊነት መሠረት ያደረገ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር አስተሳሳሪ የወል ትርክት የመገንባት ተግባር ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን የሕገ መንግሥትና ፌዴራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኃይለኢየሱስ ታዬ (ዶ/ር) ገለጹ። ህብረ ብሔራዊነትን ማጎልበት ሀገራዊ አንድነትን፣ ሰላምንና የልማት ዕድገትን ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑንም ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት። ኢትዮጵያ በህብረ ብሔራዊነት የደመቀች ለሀገራዊ እሴቶች እና ግቦች የሚተጉ እንዲሁም በጋራ እጣ ፈንታ የተሳሰሩ ህዝቦች ያሏት ሀገር ናት። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት ኃይለኢየሱስ ታዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያን ብዝሃነት እና ህብረ ብሔራዊነት ለወል ትርክት ግንባታ በማዋል አስተሳሳሪ ትርክት ከመገንባት አኳያ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊ ብዝሃነት ያላት ሀገር መሆኗን ጠቁመው፤ ይህንን ብዝሃነት በተገቢው መንገድ ማስተናገድ የጋራ ሀገራዊ ማንነትን ለመገንባት መሠረት መሆኑንም አክለዋል። በዚህም ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊነት በተገቢው በመመራቱ ለሀገር ጥንካሬ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ህብረ ብሔራዊነት አንዱ የሀገራዊ ትርክት ግንባታ ማዕከል መሆኑን ገልጸው፤ ሁሉም ቋንቋዎች፣ ባህሎችና ማንነቶች ለሀገር ግንባታ ወሳኝ መሆናቸውን ተናግረዋል። አሰባሳቢ ትርክት በሀገራዊ ስኬቶች፣ በልማትና በሀገሪቷ ህብረ ብሔራዊነት ላይ ሊመሠረት እንደሚችልም ነው ጨምረው የገለጹት። የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከባበር የኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊነት ጎልቶ የሚታይበት ብቻ ሳይሆን ሀገራዊ አንድነት የሚጠናከርበት መሆኑን ጠቁመዋል። ማዕከሉ የኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ግንዛቤ በመፍጠር በኩል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። የፌዴራል ሥርዓቱ የሚጠይቀው ዕውቀት፣ ክህሎትና አስተሳሰብ እንዲጎለብትም በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ፌዴራሊዝም በብዝሃነት የተገነባች ሀገር ውስጥ የተለያዩ ማንነቶችን አሳታፊ በሆነ መንገድ ለማስተናገድና የጋራ ሀገር ግንባታን ለማጠናከር ጠቃሚ ሥርዓት መሆኑንም ተናግረዋል። አክለውም የፌዴራሊዝም ሥርዓቱ የተለያዩ አካባቢዎች ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩና አካባቢያቸውን እንዲያለሙ ዕድል በመስጠት የልማት አቅሞችንና ፍላጎቶችን ለማስታረቅ አግዟል ብለዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ በብዝሃነት ውስጥ አብሮ የመኖር ልምድ ማካበቱንና ይህንን የአብሮነት እሴት ወደ ሀገራዊ የጋራ እሴትነት ለማሸጋገር በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቁመው፤ ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ስለሆነም ህብረ ብሔራዊነትን ከፌዴራሊዝም እና ከዴሞክራሲ እንዲሁም ከልማትና ከሀገራዊ እሴቶች ጋር በማጣመር የጋራ ሀገራዊ ማንነትና አንድነትን ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
አዲሱ ዓመት ተጨማሪ ዲፕሎማሲያዊ ድሎችን ለማስመዝገብ የበለጠ የምንሰራበት ነው
Sep 9, 2026 205
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦አዲሱ ዓመት ባለፈው ዓመት ከተመዘገቡት ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች በመነሳት ተጨማሪ ድሎችን ለማስመዝገብ፣ አዲስ ዕይታን ለመላበስና አዲስ ክህሎትን ለማዳበር ትልቅ አጋጣሚ የሚፈጥር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳም ተስፋዬ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ጳጉሜን 4 የኅብር ቀንን ‘’ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ" በሚል መሪ ሐሳብ በጋራ አክብረዋል፡፡ በበዓሉ ሥነ-ሥርዓት ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም የጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች ተገኝተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳም ተስፋዬ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፤ በተጠናቀቀው ዓመት በመሠረተ ልማት፣ በኢኮኖሚ፣ በአካባቢ ጥበቃና በዲፕሎማሲ ዘርፎችና በሌሎችም ከፍተኛ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። የጳጉሜን ቀናት እመርታን፣ ማንሠራራትን፣ ጽናትን፣ ኅብርንና ነገን በማሰብ ስኬቶችን የምንቆጥርበት እንዲሁም ለአዲሱ ዓመት አዲስ ራዕይ የምንሰንቅበት ወቅት ነው ሲሉም አብራርተዋል። የተመዘገቡትን የዲፕሎማሲ ስኬቶች መሠረት በማድረግ በአዲሱ ዓመት ለላቀ ውጤት እና ለተጨማሪ ድሎች በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።
ግብጽ ጊዜው ያለፈበትን አካሄድ በመተው በአባይ ወንዝ ላይ ያለውን አዲስ እውነታ መቀበል አለባት-ቲቦር ናጊ
Sep 9, 2026 267
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ግብጽ ጊዜው ያለፈበትንና ዘመኑን የማይመጥን አካሄድ ትታ በአባይ ወንዝ ላይ ያለውን አዲስ እውነታ መቀበል አለባት ሲሉ የቀድሞው የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቲቦር ናጊ ገለጹ። የቀድሞው የአሜሪካ ዲፕሎማት አባይን በተመለከቱ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ቆይታ ማድረጋቸውን በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል። ግብፅ አሁን ያለንበት ዘመን 19ኛው እና 20ኛው ክፍለ ዘመን ሳይሆን 2026 መሆኑን በውል ከተገነዘበች ከኢትዮጵያ ጋር አባይን በተመለከተ ሁለቱንም ወገኖች አሸናፊ የሚያደርግ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻል አፅንኦት ሰጥተው መናገራቸውን አመልክተዋል። ቲቦር ናጊ ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ጋር በቅርቡ በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን በውሃ ሃብቷ የመልማት መብት ግብጽ ልታከብር እንደሚገባ ገልጸዋል። የቀጣናው ፖለቲካዊ ገጽታ ከፍተኛ ለውጥ ማሳየቱን የገለጹት ቲቦር ናጊ፣ ግብፅ በአሁኑ ሰዓት አዲስ የኃይል ሚዛን መፈጠሩንና ኢትዮጵያም እጅጉን ማደጓን ልትገነዘብ እንደሚገባ አስምረውበታል። ግብፅ የድርድር አቀራረቧን ዳግም በመመርመርና አዲስ እና አዎንታዊ አመለካከት ይዛ ወደ ንግግር ጠረጴዛው ከተመለሰች ዘላቂና ፍትሃዊ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻልም ነው ያነሱት። የሁሉንም የተፋሰሱ ሀገራት የውሃ ሀብቶችን የመጠቀም መብት እውቅና መስጠት ላይ የተመሰረቱ ውይይቶች የጋራ መግባባት ሊፈጥሩ እንደሚችሉም ተናግረዋል። ቲቦር ናጊ የኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሃብት መጠቀም ራስ ወዳድነት ወይም በግብፅ ላይ የህልውና አደጋ ተደርጎ መታየት የለበትም ሲሉ አስገንዝበዋል። አገራት የራሳቸውን የተፈጥሮ ሃብት ይጠቀማሉ። ሁሉንም ነገር በእውነታው ላይ ቆመን እንመልከት ብለዋል። የቀድሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቲቦር ናጊ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት በተመለከተም ሀሳባቸውን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ፍትሃዊና ሕጋዊ ጥያቄ መሆኑን የገለጹት ቲቦር ናጊ፣ የጎረቤት ሀገራት የኢትዮጵያን ፍላጎቶች በሚገባ መረዳት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ትውልዱ በጀግኖች መስዋዕትነት የቆየችውን ሀገር ከነክብሯ የማጽናት አደራ አለበት
Sep 8, 2026 417
ዲላ፤ ጳጉሜን 3/2018 (ኢዜአ)፡-ጀግኖች ለሀገራቸው ዋጋ ከፍለው ያቆዩዋትን ኢትዮጵያ የዛሬው ትውልድ ከነክብሯ የማጽናት አደራ አለበት ሲሉ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገለጹ። ጳጉሜን-3 የጽናት ቀን በጌዴኦ ዞን እና በዲላ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል። የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘመናት ጸንታ የኖረችና በቅኝ ግዛት ያልተገዛች የጥቁር ህዝቦች ኩራት ናት። በውስጥና በውጭ ጠላቶች በየዘመናቱ ኢትዮጵያን ለመበታተንና ለማፍረስ የተደረገው ጥረት በቁርጥ ቀን ልጆቿ ጽናትና የደም ዋጋ ጭምር ማክሸፍ ተችሏል ብለዋል። ይሁንና ዛሬም ባንዳና ባዳ ሀገራችን ኢትዮጵያን ለማዳከም ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተባብረው እየሰሩ መሆኑን ያስታወሱት ዋና አስተዳዳሪው፣ በየዘመናቱ ጀግኖች ለሀገራቸው ዋጋ ከፍለው ያቆዩዋትን ኢትዮጵያ የዛሬው ትውልድም ከነክብሯ ማጽናት አደራ አለበት ብለዋል። በዚህም ትውልዱ በተለይ ወጣቱ የአካባቢውን ሰላም ከመጠበቅ ባለፈ ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት የሚያደርገውን ጥረት ማጠናከር አለበት ሲሉ አሳስበዋል። ጀግኖች አባቶች የደምና አጥንት ዋጋ ከፍለው ሉዓላዊነቷ የተከበረ ሀገር ለእኛ አስረክበውናል ያሉት ደግሞ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ናቸው። ዛሬ የጽናት ቀን ሲከበር ከአባቶቻችን መስዋዕትነትና ጽናት በመማር ከድህነት የተላቀቀች ሀገር ለመገንባት በየዘርፉ በሚደረገው ጥረት በንቃት በመሳተፍና በማገዝ መሆን አለበት ብለዋል። ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በተሰማራበት መስክ ለሀገሩ በጽናት በመቆም ሕብረ ብሔራዊ አንድነቷና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማሻገር የበኩሉን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአከባበሩ ላይ የተገኙት የዲላ ከተማ ነዋሪው አቶ አለማየሁ ጅግሶ በበኩላቸው፤ የጽናት ቀን ሲከበር ለህዝቦች ሰላምና ለሀገር ሉዓላዊነት መስዋዕትነት የከፈሉ ባለውለታዎችን በማሰብ መሆኑ ተገቢ ነው ብለዋል። ለከተማቸው ዘላቂ ሰላም ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ለማስቀጠል የበኩላቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።
የሀገርን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በጽናት እየተጋን ነው
Sep 8, 2026 338
ድሬዳዋ፤ ጳጉሜን 3/2018 (ኢዜአ)፡-የሀገርን ሉአላዊነት፤ ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በጽናት እየተጉ መሆናቸውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፀጥታ አባላት ገለጹ። በድሬዳዋ የሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፀጥታ አባላት የፅናት ቀንን በወታደራዊ ትርዒትና በሌሎች ስነ ስርአቶች አክብረዋል። በቀኑ አከባበር ላይ የተሳተፉት የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የጸጥታ አባላት ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የሀገርን ሉአላዊነትና ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከመቼውም ጊዜ በላይ በጽናት እየተጉ ነው። በዚህም ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት መካከል መቶ አለቃ ማማሩ ታዬ እንዳስታወቁት፤ሠራዊቱ አንድነቱንና ህዝባዊነቱን ጠብቆ የሀገርን ሉአላዊነት ለማፅናት ተጋድሎውን አጠናክሯል። ሠራዊቱ ከአባቶቹ የወረሰውን ጀግንነት በማስቀጠል የኢትዮጵያን ከፍታ ለማፅናት በቁርጠኝነት እየተጋ መሆኑን አስታውቀዋል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገርን ሉአላዊነት ከውጭና ከውስጥ ጠላቶች የመጠበቅ ተልዕኮውን በቁርጠኝነት እየተወጣ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አስር አለቃ ምህረትዓለም ባደለ ናቸው። የፅናት ቀን መከበሩ ሠራዊቱ ለሀገር መከበር ለከፈለው መስዋትነት እውቅናን በመስጠቱ ሰራዊቱ ግዳጁን በታላቅ ጀብድ ለመወጣት እንደሚያነሳሳው ጠቁመዋል። የፅናት ቀን ሰላምና ፀጥታ በአስተማማኝ መንገድ የመጠበቅን ተልዕኮ በላቀ ደረጃ ለመወጣት ቃላቸውን ያደሱበት መሆኑን ያነሱት ደግሞ የፌደራል ፖሊስ አባል ዋና ሳጅን ጠብቀው መርድ ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አባል ኮንስታብል ቅድስት ውብሸት በበኩላቸው፤ የፀጥታ መዋቅሮች ከህብረተሰቡ ጋር ትስስራቸውን በማጠናከር የነዋሪውን ሰላምና ፀጥታ በማረጋገጥ በላቀ ብቃት እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በእለቱ ሀገርን በማፅናት እና ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ ተግባራት ላይ አበርክቶ ላላቸው ተቋማት የተዘጋጁ ሽልማቶች ተበርክተዋል።
የሀገርን ሰላምና ልማት ቀጣይነትን የማረጋገጥ ተልዕኳችንን በጽናት እንወጣለን
Sep 8, 2026 349
ሀዋሳ፤ ጳጉሜን 3/2018 (ኢዜአ)፡-የሚቃጡ የጠላት ሴራዎችን በቅንጅት በማክሸፍ የሀገር ሰላምና ልማት ቀጣይነትን የማረጋገጥ ተልዕኳቸውን በጽናት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን የአገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌደራል ፖሊስ አመራሮች ገለጹ። ''በፅናት ችግርን እንሻገር፤ በአንድነት የተሻለች ሀገር እንገንባ'' በሚል መሪ ሀሳብ የ''ፅናት ቀን'' በሲዳማ ክልል ደረጃ በሀዋሳ ከተማ በተለያዩ መርሀ ግብሮች ተከብሯል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌደራል ፖሊስ አመራሮች የሀገር ሰላምና ልማት ቀጣይነት እንዲረጋገጥ ከውጭም ከውስጥም የሚቃጡ የጠላት ሴራዎችን በቅንጅት የማክሸፍ ተልዕኳቸውን በጽናት ለመወጣት ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል። የሀገርን ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የሠራዊት አባላት ሚናቸውን አጠናክረው እንደሚወጡም ተናግረዋል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት የደቡብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የጠቅላላ አገልግሎት መምሪያ ሃላፊ ኮሎኔል የሽዋስ ደምሴ እንደተናገሩት፤ የሠራዊት አባላት ለሀገር ሉአላዊነት መከበር በጽናት የሚከፍሉት የሕይወት ዋጋ መተኪያ የሌለው ነው። የሠራዊቱ አባላት የሀገር ዳር ድንበርና ሉአላዊነትን በማስጠበቅ ግዙፍ የልማት ግቦች እንዲሳኩ በጽናት ሲሰራ መቆየቱን አስታወሰዋል፡፡ በጽናት መቆም ለወታደር ብቻ የሚተው አይደለም ያሉት ኮሎኔል የሽዋስ፣ ሁሉም ለሀገር ሰላምና እድገት በጽናት በመቆም የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አለበት ብለዋል። በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የደቡብ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ መምሪያ የሰው ሀብት ሥራ አመራር ምክትል መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ሲሳይ ገላን በበኩላቸው፣ የሀገር ሰላምና ልማትን በዘላቂነት አጠናክሮ ለማስቀጠል ሠራዊቱ ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው ብለዋል ። በፀረ ሰላም ሀይሎች የሀገርና የህዝብ ሰላም እንዳይታወክ ለመከላከል የፌደራል ፖሊስ አባላት ሁልጊዜ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸው፣ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ እንዲፋጠን በየጊዜው የሚቃጡ የጠላት ሴራዎችን በቅንጅት የማክሸፍ ተልዕኮን በጽናት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ህዝቡ የልማት ተሳትፎውን እንዲያጠናክር የፖሊስ አባላት ሰላምን በዘላቂነት የማስጠበቅ ተልዕኳቸው ላይ አተኩረው እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የጽናት ቀንን ስናከብር ውስብስብ ፈተናዎች አልፋ በብልጽግና ጉዞ ላይ ያለችውን ኢትዮጵያ ልማቷን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለንን ጽናት በማረጋገጥ መሆን አለበት ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ ዳዊት ዳንጊሶ ናቸው። ጀግኖች አባቶች በከፈሉት መስዋዕትነት ነጻነቷ ተጠብቆ የቆየችውን ኢትዮጵያ ልማቷን በማፋጠን ለቀጣይ ትውልድ ያደገች ሀገር ለማስረከብ ሰላሟን በጋራ ልናጸና ይገባል ብለዋል። የተጀመሩ የልማትና የብልጽግና ግቦችን ከዳር ለማድረስ ፖሊስ ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በተናበበ መልኩ በጽናት የሚያደርገውን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክር የገለጹት ደግሞ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ተስፋዬ ዴቢሶ ናቸው።
ማህበራዊ
የኢትዮጵያ ጥንካሬ በብዝሃነትና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት ላይ የፀና ነው
Sep 9, 2026 131
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጥንካሬ በብዝሃነትና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት ላይ የፀና መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ፡፡ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጳጉሜን 4 "የሕብር ቀን"ን በማስመልከት ልዩ የኪነ-ጥበብ ምሽት አከናውኗል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ ሚኒስትሮች፣ የሥራ ኃላፊዎች፣ ተጋባዥ እንግዶችና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል፡፡ የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ ህልውናና ጥንካሬ በብዝሃነት፣ በህብረ-ብሔራዊ አንድነት ላይ የሚጸና መሆኑን አስረድተዋል። የቀደሙ አባቶችና እናቶች አብሮነታቸውን አጎልብተው ያቆዩልንን ሀገር፣ እኛም በአንድነት ተጠናክረን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ ቃላችንን የምናድስበት ወቅት ነው ብለዋል። በጋራ ህልውናዋን ጠብቀንና ከፍ አድርገን ለትውልድ ማስተላለፍ የሁላችንም ሃላፊነት መሆኑን አብራርተዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፀጋዬ ማሞ በበኩላቸው፤ ህብር የብዙ ልዩነቶች ድምር ውጤትና የአንድነት ጥንካሬ በመሆኑ፣ አዲሱን ዓመት ስንቀበል የመደመር፣ የመደጋገፍና የፍቅር መንፈስን በማንገብ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ የባህሎች፣ የቋንቋዎችና የእምነቶች መኖሪያ በመሆኗ ይህ ህብረ-ብሔራዊነት የታላቅነትና የውበት ምስጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን በርካታ ፈተናዎች ማለፍና ተሻጋሪ ዕቅዶችን ማሳካት የተቻለውም ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው በጋራ ዓላማ በመቆም ብቻ እንደሆነ አስረድተዋል።
በአዲሱ ዓመት የማዕድ ማጋራትና የመደጋገፍ ባህልን ይበልጥ ማጎልበት ወሳኝ ነው
Sep 9, 2026 101
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲሱ ዓመት የማዕድ ማጋራትና የመደጋገፍ ባህልን ይበልጥ ማጎልበት እንደሚገባ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ጌታቸው በዳኔ ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የዘመን መለወጫ በዓልንና የሕብር ቀን ምክንያት በማድረግ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የሴቶች ማረፍያና ልማት ማኅበር ለሚገኙ ሴቶች ማዕድ አጋርቷል። በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትር አማካሪ ጌታቸው በዳኔ በዚሁ ወቅት በሕብር ቀን ሚኒስቴሩ ለስርዓተ ጾታ እኩልነት እና ለማህበራዊ ደህንነት መረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ለሀገር እድገት፣ ሰላምና ማህበራዊ መረጋጋት ከሚሰጡ ቅድሚያዎች መካከል አንዱ የሴቶችን መብት ማስከበር እንደሆነ አመልክተዋል። የሴቶችን መብት ለማስጠበቅ ከሚደረገው ጥረት ጎን ለጎን፣ በተለያዩ ምክንያቶች ለጥቃትና ለችግር የተጋለጡ ሴቶችን የማህበራዊና ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በዘላቂነት መልሶ ለማቋቋም የሚያግዙ ተግባራትን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እያከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ በዛሬው ዕለትም በተለያዩ ምክንያቶች ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ማረፊያና ልማት ማኅበር የአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በዓይነትና በገንዘብ ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡ የሕብር ቀን አብሮነትንና ማህበራዊ ትስስርን ይበልጥ የሚጠናከርበትና የመደጋገፍ እሴትን በተግባር የሚገለጥበት መሆኑን ተናግረዋል። የዛሬው ማዕድ ማጋራትም እርስ በእርስ የመረዳዳት ባህል የሚያሳይ፣ አዲሱን ዓመት በተስፋ፣ በደስታ እና በሙሉ ስነ-ልቦናዊ ዝግጅት ለመቀበል እንዲያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ የተደረገው የበጎ አድራጎት ተግባርም ይህንን ታሪካዊ እሴት በመጠበቅ ለሚመጣው ትውልድ ለማስተላለፍ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። የሴቶች ማረፍያና ልማት ማኅበር ዋና ዳይሬክተርና መስራች ማርያ ሙኒር በበኩላቸው፤ በተደረገው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸው፣ ለዚህም በተጠቃሚዎች ስም ምስጋና አቅርበዋል።
በአብሮነትና በተደመረ አቅም ወገኖችን ማገዝ፣ ትውልድን መገንባትና ሀገርን ማፅናት እንደሚቻል በተግባር እየታየ ነው
Sep 9, 2026 79
ሠመራ፤ ጳጉሜ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአብሮነትና በተደመረ አቅም ወገኖችን ማገዝ፣ ትውልድን መገንባትና ሀገርን ማፅናት እንደሚቻል በተግባር እየታየ መሆኑን የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኡመር ኑር ገለጹ። ጳጉሜን 4 "የሕብር ቀን" "ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ" በሚል መሪ ሃሳብ በአፋር ክልል ሠመራ ከተማ በጎ ተግባራትና ድጋፍ በማድረግ ተከብሯል። መርሃ ግብሩ የደም ልገሳ በማድረግ፣ የትምህርት ቁሳቁስና ሌሎችም ድጋፎች እንዲሁም በዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል ታካሚዎችን በመጠየቅ፣ ማዕድ ማጋራትና ነፃ የሕክምና አገልግሎት መስጠት ተችሏል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድና የመሬት ቢሮ ኃላፊ ኡመር ኑር፤ እለቱን በሰብአዊነትና መልካም ተግባራትን በማከናወን ማክበር መቻሉ ሁላችንንም ያስደሰተ ተግባር ነው ብለዋል። በአብሮነትና በተደመረ አቅም ወገኖችን ማገዝ፣ ትውልድን መገንባትና ሀገርን ማፅናት እንደሚቻል በተግባር እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው እለትም የተከናወነው ተግባር የዚሁ ማሳያ መሆኑን አንስተው መሰል ተግባራት ባህል ሆነው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መሐመድ ዓሊ፤ የኢትዮጵያዊያን የመተጋገዝ፣ መረዳዳትና አብሮነትን የማጠናከር ተግባር ባህል ሆኖ መቀጠሉን አንስተዋል። በዚሁ መሰረት የህብር ቀንን ምክንያት በማድረግ በአፋር ክልል የተለያዩ በጎ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸው በሰመራ ከተማ የታመሙ ወገኖችን በመጠየቅ፣ ድጋፍ በማድረግና ደም በመለገስ መከበሩን ተናግረዋል። በእለቱ የችግኝ ተከላ፣ የደም ልገሳ፣ የትምህርት ቁሳቁስና የንጽህና መጠበቂያ ድጋፍ እንዲሁም በዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል ታካሚዎችን በመጠየቅ ማእድ ማጋራት ተችሏል ብለዋል።
የሕብር ቀን ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የአብሮነት እሴቶችን ለማጠናከር አይነተኛ ድርሻ አለው - ከንቲባ ከድር ጁሃር
Sep 9, 2026 69
ድሬዳዋ፣ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፡-የሕብር ቀን ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የአብሮነት እሴቶችን ለማጠናከር አይነተኛ ድርሻ ማበርከቱን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። በድሬዳዋ ጳግሜን-4 "የሕብር ቀን" ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያስቀጥሉ የበጎ ተግባራት ሥራዎች ተከብሯል። ቀኑን ምክንያት በማድረግ ለተቸገሩ ወገኖችና፣ ለተማሪዎች እንዲሁም ለመቄዶኒያ የአረጋዊያን መርጃ ማዕከል ድጋፍ ተደርጓል። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር በወቅቱ እንዳሉት የሕብር ቀን መከበር ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የአብሮነት እሴቶችን ለማጠናከር አይነተኛ ድርሻ አለው። አስተዳደሩ የአብሮነትና የእርስ በርስ መረዳዳት እሴቶችን በማጠናከር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ለማሳካት አበክሮ ሲሰራ መቆየቱንም ጠቁመዋል። በተለይም የአብሮነትና የአንድነት እሴቶችን በማጠናከርና ሰው ተኮር ልማትን በማስፋፋት ማህበራዊ ኃላፊነቶችን መወጣት ላይ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። በቀጣይም ይህን መልካም ተግባር በማስቀጠል ለትውልድ የምትመች ሀገርን ለማስረከብ በጋር መስራት ይገባል ብለዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ በበኩላቸው ብዝሀነት ለልዩነት ሳይሆን በጋራ ለማደግ መሰረት መሆኑን ተናግረዋል። ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ትርክት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ የሕብር ቀን መከበሩ የህብረተሰቡን አብሮነት ለማጎልበት ያግዛል ብለዋል። በተለይ ቀኑን ምክንያት በማድረግ የህብረተሰቡን የመረዳዳት እሴቶች በመተግበር ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን መርዳት መጀመሩ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። በመርሀ ግብሩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አብዲ ሙክታርን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችም ተሳታፊ ሆነዋል።
ኢኮኖሚ
የግብርናና የምግብ ሥርዓትን ማጠናከር ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት ወሳኝ ነው
Sep 9, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦የግብርናና የምግብ ሥርዓትን ማጠናከር አፍሪካ የአየር ንብረት ጫናን በመቋቋም ዘላቂ ልማቷን እንድታሳድግ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ ከጳጉሜን 2 እስከ 4 ቀን ሲካሄድ የቆየው አህጉራዊ ጉባኤ ፍጻሜውን አግኝቷል። በጉባኤው ወቅት በአፍሪካ የግብርናና የምግብ ሥርዓትን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በማጣጣም የሕዝቦችን የምግብ ዋስትና እና የኑሮ ጽናት ለማሻሻል የሚያስችሉ ዋና ዋና አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በዚሁ መድረክ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን የአህጉሪቱን የግብርናና የምግብ አጀንዳ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ውይይቶች የበለጠ ማስገንዘብና ውሳኔዎችንም ወደ ተግባር ማሸጋገር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ህብረት (Alliance for Food Sovereignty in Africa - AFSA) አስተባባሪ ዶክተር ሚሊዮን በላይ እንደገለጹት፤ አፍሪካ በግብርናና በምግብ ሥርዓት ያላትን የራሷን ልምድና መፍትሔ በማጠናከር በአህጉርና በዓለም አቀፍ መድረኮች የራሷን አጀንዳ በተግባር ማስፈጸም ይገባታል። አህጉሪቱ በዘርፉ ያላትን መልካም ተሞክሮ የበለጠ ማጉላት እንዳለባት ጠቁመው ለተቋቋሚ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አግሮ-ኢኮሎጂን ማስፋፋት፣ የገበሬዎችን የዘር ሀብት መጠበቅና የገበሬዎችን ተሞክሮ ከሳይንስ ጋር በማጣመር የተሻለ የግብርና ልማት ማምጣት እንደሚገባ አስረድተዋል። በተጨማሪም የአፈርና የውሃ ሀብትን በአግባቡ መጠቀም፣ የአካባቢ የምግብ ገበያዎችን ማጠናከርና አፍሪካ የምግብ ፍላጎቷን በተቻለ መጠን በራሷ ምርትና ሀብት በመሸፈን የምግብ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ እንደሚገባት ገልጸዋል። የምግብ ሥርዓቱ ቀጥተኛ ተዋናዮች ሀሳባቸው በውሳኔዎች ውስጥ እንዲንጸባረቅ የሚያስችል ተጨባጭ ተሳትፎ ሊኖራቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ በዘር ሀብት ጥበቃ፣ በአግሮ-ኢኮሎጂና በምግብ ሉዓላዊነት ያላትን ልምድ በማጠናከር ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ ማካፈል እንደምትችል ጠቁመዋል፡፡ የአርሶ አደሮችን የዘር ሀብት መጠበቅና አሀጉራዊ ተሞክሮዎችን ከሳይንሳዊ እውቀት ጋር በማጣመር የተሻለ የግብርና ልማት ለማስመዝገብ መስራት እንደሚገባ አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዕዳ ተላቆ ወደ ውጤታማ የትርፋማነት ምዕራፍ ተሸጋግሯል - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ
Sep 9, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከነበረበት ዕዳ ተላቆ ወደ የትርፋማነት ምዕራፍ መሸጋገሩን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞቹ በተገኙበት የዘንድሮውን የ2018 በጀት ዓመት "ንጹህ ኢነርጂ ለተሻለ ሕይወት" በሚል መሪ ሐሳብ የተቋም ቀኑን አክብሯል። ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በዚህ ወቅት፤ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢትዮጵያን የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል የማድረግ ራዕይ የሚያሳካ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በ2018 በጀት ዓመት በርካታ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን፣ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በመሥራት ተቋማዊ የመፈጸም አቅምን ማላቅ መቻሉን አስታውቀዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የአሰላና የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ ኃይል የማመንጨት አቅምን ወደ 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት በማሳደግ የ23 በመቶ ዕድገት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ተናግረዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ጠቅላላ የኃይል ምርት አቅም 35 ሺህ 671 ጊጋ ዋት በሰዓት በማድረስ የ124 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘት እንደተቻለ አስረድተዋል። ከኃይል ሽያጭና ዳታ ማይኒንግ 475 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ መገኘቱም የተቋሙን የገቢ አቅም ከባለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ64 በመቶ ዕድገት እንዲመዘገብ አስችሏል ብለዋል። በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ 39 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ በማስመዝገብ ተቋሙ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዕዳ ወደ ትርፋማነት የተሸጋገረበትን ስኬታማ ዘመን እንዳሳለፈ ጠቅሰዋል። በዚህም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከነበረበት ዕዳ ተላቆ ወደ ውጤታማ የትርፋማነት ምዕራፍ መሸጋገሩን አብስረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ላስመዘገበው ስኬትም የተቋሙ አመራር፣ ሠራተኞችና ባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ መሆኑን በማንሣት ለዚህ ሁሉንም አመስግነዋል። ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የሁሉም ዜጎች ኩራትና አሻራ ያረፈበት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ በይፋ የተመረቀበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑንም አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ቀንም የሕዳሴን ታሪካዊ ፍጻሜ በመዘከር የላቀ አፈጻጸም ለነበራቸው አመራርና ሠራተኞች ዕውቅና ለመስጠት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በየዓመቱ ጳጉሜን 4 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ቀን ሆኖ እንደሚከበር አስታውቀዋል።
የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ የኢትዮጵያን የመሰረተ ልማት ስራዎች ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋገጠ
Sep 9, 2026 77
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ):- የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ የኢትዮጵያን የመሰረተ ልማት አጀንዳዎች እንደሚደግፍ አስታወቀ። የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ አዲሷን የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ (AIIB) ፕሬዝዳንት ዙ ጂያዪን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተሳትፈዋል። የሁለቱ ወገኖች ውይይት ባንኩ በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተሳትፎ ጨምሮ በአበይት የኢትዮጵያ የልማት ትኩረቶች ላይ ያተኮረ ነው። ከዚህም ባሻገር በኢነርጂ ዘርፍ እና የአየር ንብረት ለውጥን በሚከላከሉ ፕሮጀክቶች ዙሪያ ያላቸውን አጋርነት ማሳደግ፣ በዝቅተኛ ወለድ የሚሰጡ የብድር አቅርቦቶችን ማመቻቸት እንዲሁም ከሌሎች ባለብዙ ወገን የልማት ባንኮች ጋር በቅንጅት መሥራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መክረዋል። በውይይቱ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ለፕሬዝዳንት ዙ ጂያዪ የኢትዮጵያ ሪፎርም አጀንዳ አፈጻጸም እና እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሉ ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ባንኩ ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጣቸውን የልማት ትኩረቶች መደገፍ የሚችልባቸውን የፋይናንስ አማራጮች አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዙ ጂያዪ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በቀጣናው የኃይል ትስስርን በማስፋት ረገድ እየተወጣች ያለውን ግንባር ቀደም ሚና አድንቀዋል። ባንኩ የኢትዮጵያን የመሰረተ ልማት አጀንዳ ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ወገኖች አጋርነታቸውን በማጎልበት፤ ዘላቂና አሳታፊ የመሰረተ ልማት ዕድገትን በጋራ እውን ለማድረግ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ (AIIB) ፕሬዝዳንት ዙ ጂያዪ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ እንደሚገኝ የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የመቻልና የአንድነት ሕብራዊነት መገለጫዎች ናቸው
Sep 9, 2026 111
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ኢትዮጵያውያን በትብብር ያሳኳቸው የመቻልና የአንድነት ሕብራዊነት መገለጫዎች መሆናቸውን የሰላም ሚኒስቴር ገለጸ። የሰላም ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ሃላፊ መብራቱ ካሳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በአንድነት ማሰሪያ የተጋመዱ ናቸው። ኢትዮጵያውያን የተጋመድን ነን ሲባል ከቃል ባለፈ በዓድዋ ጦርነትና በሌሎች ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለመዳፈር በተቃጡ ጥቃቶች ላይ በመተባበር በተግባር አሳይተናል ብለዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጋራ የላብ፣ የደምና የውሃ ጠብታ ውጤት መሆኑን በመግለጽ፤ የኢትዮጵያውያን በጋራ መቻልን ያሳያል ብለዋል። ኢትዮጵያውያን ከማንኛውም አካል ተፅዕኖ ነጻ በመሆን ራሳቸውን በራሳቸው መለወጥ ማሳደግና ማበልጸግ እንደሚችሉ ያሳዩበት የሕብራዊነት መገለጫ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በህዝቦች መካከል የዘመናት ቁርሾ ሆነው የቆዩ ልዩነቶችን በምክክር መፍታት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን የጋራ ችግራቸውን በራሳቸው አቅም በምክክር ለመፍታት ያሳዩት ቁርጠኝነት ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸውን ቀናኢነት ያሳያል ብለዋል። ሀገራዊ ምክክር ጉባዔው ኢትዮጵያ የራሷን ችግር በራሷ እየፈታች ያለች ሀገር መሆኗን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በተግባር ያረጋገጠ መሆኑንም ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማትን በማስፋት አንድነትንና ልማትን የሚያጠናክር ነገን እየገነባን ነው
Sep 9, 2026 186
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማት በማስፋት አንድነትና ልማትን የሚያጠናክር አውድ መፍጠር የሚያስችል ነገን እየገነባን ነው ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከሌሎች የፌዴራል ተቋማት ጋር በመተባበር ነገ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከብረውን የ"ነገ ቀን" በማስመልከት መግለጫ ሰጥቷል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መንግሥት የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች እያከበረ ይገኛል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር በዲጂታል ኢኮኖሚ የዳበረች ኢትዮጵያን ለማስረከብ የሚከናወኑ ተግባራትን የሚያሳየው የነገ ቀን ይከበራል ብለዋል። ኢትዮጵያ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን በመቅረጽ የዲጂታል ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሥራ እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። በዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም የጎለበተ፣ ዘመኑን የዋጀ ሲቪል ሰርቪስ በመገንባት፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት በመስጠት ምን ዓይነት ነገን እንገንባ በሚለው ላይ መሠረት እየጣልን ነው ብለዋል። ነገ ማለት ወጣቶች የሚረከቧት ኢትዮጵያ ማለት ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ለትውልዱ የአንድነት፣ የሰላምና የልማት አውድ መፍጠር የሚያስችል ነገን ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል። አዲስ ዓመት አዲስ ተስፋና ሀሳብ መፈጠሪያ መሆኑን ገልጸው፤ ለሕዝባችን የገባነውን ቃል በተግባር መፈጸም ይገባናል ብለዋል። አዲሱ ዓመት ፈተናዎችን አልፈን የተሳካ ሰላምና ልማት የምናስመዘግብበት እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት እያከናወነች ያለችው ውጤታማ ተግባር ለቀጣናው የዲጂታል ትብብር በተሞክሮነት የሚጠቀስ ነው
Sep 9, 2026 179
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 4 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሳይበርና መረጃ ደህንነት እያከናወነች ያለችው ውጤታማ ተግባር ለቀጣናው የዲጂታል ትብብር በተሞክሮነት የሚጠቀስ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ መንግሥታት በይነ-መንግሥታዊ ባለሥልጣን (ኢጋድ) ገለጸ። የኢጋድ የኢኮኖሚ ትብብርና ቀጣናዊ ውህደት ዳይሬክተር ሙሂየልዲን አልቶሃሚ ጠሃ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያካበተችው ተሞክሮ ለኢጋድ አባል ሀገራት የተሻለ ትምህርት የሚሰጥ ነው። በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ባደረጉት ጉብኝት በሳይበር ደህንነት፣ በዳታ ጥበቃና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ለቀጣናዊ የእውቀት ሽግግር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸው መገንዘባቸውን ተናግረዋል። ኢጋድ በአሁኑ ወቅት እያዘጋጀው የሚገኘው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕቀፍ የአባል ሀገራትን የዘርፉ ፖሊሲ፣ የመረጃ ጥበቃና የአጠቃቀም ሥነ-ምግባር፣ ተቋማዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ልማትና የእውቀት ሽግግር ላይ አተኩሮ እንደሚሠራ አስረድተዋል። የኢጋድ አባል ሀገራት በዘርፉ ያለባቸውን የአቅም ክፍተት ለመሙላትና ቀጣናዊ ልማትን ለማፋጠን እንደ ኢትዮጵያ የተሻለ አቅም ካላቸውና ውጤታማ ተግባር እያከናወኑ ከሚገኙ ሀገራት ልምድና ተሞክሮ መውሰድ እንዳለባቸው አሳስበዋል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቀጣናው በተለይም በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርት እንዲሁም በሰላምና ደህንነት ዘርፎች የሚከናወኑ የልማት ተግባራትን ለማገዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አመልክተዋል። የቴክኖሎጂውን ጥቅም በስፋት ለማጎልበት የሰው ኃይል ልማትን ማጠናከር፣ ቀጣናዊ ትብብርን ማሳደግና የእውቀት ሽግግር ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የቴክኖሎጂ ባለሙያው ሰለሞን ካሳ በበኩሉ፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እንደ ጤና እና ግብርና ያሉ ዘርፎችን ለመደገፍ ብሎም እንደ ድርቅ ያሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን አስቀድሞ በመተንበይ ምርታማነትና ዕድገትን እንደሚያፋጥን ገልጿል። ኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት በማቋቋም፣ ፖሊሲ በመንደፍ እና ምርምሮችን በማካሄድ ለአጎራባች ሀገራት ጭምር አርዓያ የሚሆን ተግባር እያከናወነች መሆኑንም ተናግሯል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ፤ የመጪው ዘመን የኢኮኖሚ ማንሰራራት መሰረት
Sep 7, 2026 211
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 2/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ጉልህ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ትገኛለች። ባለፉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከትሎም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ይፋ መደረጉ ይታወቃል። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂም ሁሉን አቀፍ እና ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሚመራ ጠንካራ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለመ ነው። ይህም ፈጠራን፣ ምርምርን፣ ስታርት አፕን በማበረታታት፣ የሞባይልና ኢንተርኔት ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር በመጨመር የፋይናንስ አካታችነትን ያረጋገጡ የቴሌብርና መሰል የዲጂታል ክፍያ አማራጮች ማኅበረሰቡ የዕለት ተዕለት አሠራር አካል የሚሆኑበትን ዕድል ፈጥሯል። በፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያና መሶብ የአንድ ማዕከል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕላትን በማበራከትም የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳርን ፈጥሯል። ይህም የተገልጋዮችን ምልልስ፣ ወጪ፣ ጉልበትና ጊዜ በመቆጠብ፣ የመንግሥት አገልግሎት ውጤታማነትን በማጎልበት እንዲሁም መልካም አስተዳደርን በማስፈን የኢትዮጵያን የብዝኅ ኢኮኖሚ ማንሰራራት ጉዞ እያሳለጠ ይገኛል። በአጠቃላይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የፐብሊክ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት፣ የሰው ኃይል አቅምና ፈጠራን በማጎልበት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠናቀቂያና «ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ባስጀመሩበት ወቅት፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የኢትዮጵያን ብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥን መሠረት መጣሉን አስታውሰዋል። የስትራቴጂው ትግበራ ሙሉ በሙሉ በስኬት መጠናቀቁም ለቀጣይ የዲጂታል ኢትዮጵያ አስተማማኝ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ የትኩረት መስክ የብዝኅ ኢኮኖሚ ሥርዓትን በማሳለጥ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማንሰራራት ጉዞ እያነጸ መሆኑን አብራርተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን በማጎልበት ሁሉም ዜጋ አካታችና ፍትሐዊ የዲጂታል መሠረተ ልማት የሚያገኝበትን ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ለዚህም በስትራቴጂው መሠረት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት፣ የኢንተርኔት ተደራሽነት፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ፣ የዲጂታል ገንዘብ ዝውውርና በተቋማት መካከል የዳታ ልውውጥ ውጤታማነት ለማሻሻል እንደሚሠራ ጠቅሰዋል። የሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ የሳይበር ደኅንነትና የዳታ አስተዳደር ላይ ትኩረት በማድረግ የወጣቶችን የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ፣ አዳዲስ ፈጠራዎችን እና የዲጂታል ሥራ ዕድሎችን ማስፋፋት የስትራቴጂው የትኩረት መስኮች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ዘመኑ የሚጠይቀው ጉዳይ በመሆኑ ኢትዮጵያ በዚህ መስክ ራሷን መቻል እንዳለባትም አስገንዝበዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ላይ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ የዲጂታላይዜሽን የትኩረት አቅጣጫ የኢኮኖሚ ማንሰራራት ጉዞውን የሚቀርጽ እመርታዊ ለውጥ አምጥቷል ብለዋል። በዚህም የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ የፈጠራቸው የኢትዮ-ኮደርስ፣ የመሶብ አንድ ማዕከል፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያና የዲጂታል ፋይናንስ ግብይቶች ፈጠራን በማበረታታት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን እያሳለጡ መሆናቸውን አንስተዋል። በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ መሠረተ ልማት ዝርጋታ ጎን ለጎን የዜጎችን ዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ሥራዎች መካከል የኢትዮ-ኮደርስ ሥልጠና ተጠቃሽ ነው። ወጣት ባዩሽ ተስፋዬና ቀለሙ ዘለቀ እንደገለጹት፤ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን የኮደርስ ሥልጠና መውሰዳቸው የዲጂታል ክህሎታቸውን በማበልጸግ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ገልጸዋል። ወጣት መሰረት አቦሰጥ እንደምትለውም፤ የኢትዮ-ኮደርስ ሥልጠና የሰው ሠራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅሟን በማጎልበት ተጠቃሚ እያደረጋት ነው። ወጣት እሸቱ አበራ በበኩሉ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በሌሎች ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ዓይነ ሥውር ዜጎችም እንደ ማንኛውም ሰው የኮደርስ ሥልጠናን መውሰድና ተጠቃሚ በመሆን ከዘመኑ ጋር መራመድ እንደሚችሉ ዕድል መፍጠሩን ገልጿል።
መሶብ የአንድ ማዕከል፤ የመደመር መንግሥት የአገልግሎት ትራንስፎርሜሽን ማስፈንጠሪያ
Sep 6, 2026 308
መሶብ የአንድ ማዕከል፤ የመደመር መንግሥት የአገልግሎት ትራንስፎርሜሽን ማስፈንጠሪያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት የተጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የዜጎችን እንግልት በመቀነስና የመንግሥት አሰራርን በማዘመን ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አሰራርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማዘመን፣ የወረቀት ስራንና እንግልትን በማስቀረት ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊና ግልጽ አገልግሎት ለመስጠት የተዘረጋ ስርዓት ነው። ፕሮጀክቱ አገልግሎት ፈላጊዎች በአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፤ ይህም ህብረተሰቡ የመሬት አስተዳደር፣ የኢንቨስትመንት፣ የገቢዎችና ሌሎችንም የመንግሥት አገልግሎቶች በኦንላይንና በአካል ማግኘት የሚያስችል ነው። አገልግሎቱ በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በባህር ዳር እና በሌሎችም የክልሎች ከተሞች ተግባራዊ መሆን የጀመረ ሲሆን፤ ማዕከላቱን በየደረጃው እስከ ወረዳ ድረስ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተንቀሳቃሽ መሶብ አገልግሎትን በአዲስ አበባ ባስጀመሩበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት የቆዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎችን በመፍታት የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውታል። ይህንን ለማሳካት በመንግሥት፣ በግል ኩባንያዎችና በእያንዳንዱ ዜጋ ዘንድ የባህልና የአስተሳሰብ ለውጥ መምጣት እንዳለበትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል። ሀገሪቷን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መንግሥት በትኩረት እየሰራባቸው ካሉ አምስት የኢኮኖሚ አምዶዎች መካከል ቴክኖሎጂ አንደኛው መሆኑን ነው በወቅቱ ያብራሩት። ቴክኖሎጂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የቱሪዝም ዘርፍን ለማዘመን እንዲሁም ዲጂታል የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ሁሉንም የልማት ዘርፎች የሚያቀናጅ ዋና መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ሲሆን፤ በተለይም የአገልግሎት አሰጣጥን ወደ ዘመናዊና ዲጂታል ሥርዓት በመቀየር የዜጎችን እንግልት መቀነስ አስችሏል። የ“ዲጂታል 2030” ስትራቴጂ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተገኙ ስኬቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሀገራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግርም አብራርተዋል። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ በሀገሪቷ ባሉ ከ108 በላይ ማዕከላት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ተችሏል። የአገልግሎቱ አጠቃላይ ሀገር አቀፍ የተገልጋዮች እርካታ መጠን ከ99 በመቶ በላይ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። በዘመናዊ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት መስጫዎች ማዕከላት በአካል መጥተው መገልገል ለማይችሉ ዜጎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንና ተደራሽነትን ይበልጥ ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አጽንኦት መስጠታቸው ይታወሳል። በመዲናዋ የተዘረጋው የዲጂታል መሶብ አገልግሎት፣ በከተማ ደረጃ እየተካሄደ ላለው የዲጂታል ሽግግር ማሳያ ከመሆኑም በላይ በነዋሪዎች ዘንድ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።
ስፖርት
የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በሰባት ስታዲየሞች ይደረጋል
Sep 9, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4 /2018 (ኢዜአ)፦ የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በተመረጡ ሰባት ስታዲየሞች እንደሚካሄድ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታወቀ። የሊጉ ጨዋታዎች የእጣ ማውጣት ስነ ስርዓት መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም ይከናወናል። መስከረም 30 የሚጀምረው የ2019 ዓ.ም የሊጉ ውድድር በተመረጡ ሰባት ሜዳዎች እና በተዘጋጁ ስድስት ቋቶች በሚወጣው እጣ መሰረት የውድድር ዓመቱ መርሃ ግብር ይዘጋጃል። አዲስ አበባ ስታዲየም፣ አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባህርዳር አለም አቀፍ ስታዲየም፣ሀላባ ስታዲየም፣ ሆሳዕና አብዩ ኤርሳሞ ስታዲየም እና አርባምንጭ ዩንቨርሲቲ አባያ ካምፓስ ስታዲየም ውድድሩ የሚካሄድባቸው ሜዳዎች ናቸው። በውድድሩ ላይ 18 ክለቦች እንደሚሳተፉ የሊጉ አክሲዮን ማህበር መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሚጀመርበት ጊዜ ላይ ማሻሻያ ተደረገ
Sep 9, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ2019 ዓ.ም የውድድር ዘመን ጥቅምት 8 ቀን 2019 ዓ.ም እንደሚጀመር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። ፕሪሚየር ሊጉ መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም እንደሚጀመር ተገልጾ ነበር። ይሁንና አብዛኞቹ ክለቦች ዝግጅት ባለመጀመራቸው እና በሴቶች ብሔራዊ ቡድኑ የኦሊምፒክ ማጣሪያ ዝግጅት ምክንያት ሊጉ የሚጀመርበት ቀን ጥቅምት 8 2019 ዓ.ም እንዲሆን መወሰኑን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል።
በካራባኦ ካፕ ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ይጫወታል
Sep 9, 2026 107
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ):- በእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ የሶስተኛ ዙር መርሐ ግብር ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ዛሬ ጨዋታውን ያደርጋል። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም ይካሄዳል። በሁለተኛ ዙር ቼልሲ ሉተን ታውንን፣ ሊድስ ዩናይትድ ኖቲንግሃም ፎረስትን በተመሳሳይ 2 ለ 0 አሸንፈዋል። ክለቦቹ በውድድሩ ታሪክ ሁለቱ ጊዜ ተገናኝተው ቼልሲ በሁለቱም ጨዋታዎች አሸንፏል። እ.አ.አ በ2001 በአራተኛ ዙር ተገናኝተው ቼልሲ 2 ለ 0 አሸንፏል። ቡድኖቹ እ.አ.አ በ2012 በሩብ ፍጻሜው ባደረጉት ጨዋታም ቼልሲ 5 ለ 1 ተጋጣሚውን ረትቷል። ከ14 ዓመታት በኋላ ዳግም በካራባኦ ዋንጫ ተገናኝተዋል። ቼልሲ የካራባኦ ዋንጫን አምስት ጊዜ ያነሳ ሲሆን ለመጨረሻ ጊዜ አሸናፊ የነበረው እ.አ.አ በ2015 ነው። ሊድስ ዩናይትድ እ.አ.አ በ1968 ውድድሩን ማሸነፍ ችሏል። ባለሜዳው ቼልሲ ጨዋታውን የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት አግኝቷል። የ39 ዓመቱ አውስትራሊያዊ ጃሬድ ጊሌት ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል።
ፒኢስጂ ከስሎቫን ብራቲስላቫ፣ ናፖሊ ከአርሰናል እና ሊቨርፑል ከአትሌቲኮ ማድሪድ፤ የዕለቱ ተጠባቂ ጨዋታዎች
Sep 9, 2026 135
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ):- በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ስድስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት አራት ሰዓት ፒኤስጂ ከስሎቫን ብራቲስላቫ በፓርክ ደ ፕሪንስ ይጫወታሉ። የፈረንሳዩ ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግን ለተከታታይ ጊዜ ያነሳ ክለብ ነው። የስሎቫኪያው ስሎቫን ብራቲስላቫ በአዲሱ የውድድር ፎርማት ለሁለተኛ ጊዜ ይሳተፋል። የአውሮፓ ታላቁን ክብር ለሶስተኛ ጊዜ ለማንሳት ያለመው ፒኤስጂ ክብሩን የማስጠበቅ ጉዞውን ዛሬ ይጀምራል። በሌላኛው መርሐ ግብር ናፖሊ ከአርሰናል በዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ስታዲየም ምሽት አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የባለፈው ዓመት የሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ተፋላሚ የሆነው አርሰናል ከጣልያኑ ክለብ በሚያደርገው ጨዋታ የሊግ ምዕራፍ ውድድሩን ይጀምራል። ናፖሊ ባለፈው የውድድር ዓመት በሊግ ምዕራፉ ላይ የተሰናበተ ሲሆን ዘንድሮ በጥሩ ሁኔታ ለመጀመር የለንደኑን ክለብ ያስተናግዳል። ምሽት አራት ሰዓት ላይ ሊቨርፑል ከአትሌቲኮ ማድሪድን በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ሊቨርፑል የስድስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ነው። አትሌቲኮ ማድሪድ ሁለት ጊዜ ለፍጻሜ ደርሶ ተሸንፏል። ጨዋታው ጠንካራ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል። ባርሴሎና ከፌይኖርድ ሮተርዳም እና ስቱትጋርት ከቫይኪንግ ኤፍሲ በተመሳሳይ ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ45 ላይ ይጫወታሉ። ምሽት አራት ሰዓት ላይ ስፖርቲንግ ሊዝበን ከጋላታሳራይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የአየር ንብረት ለውጥ በማኅበረሰብ ጤና ላይ ሊያሳድር የሚችለውን ተፅዕኖ ለመከላከል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Sep 9, 2026 115
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦የአየር ንብረት ለውጥ በማኅበረሰብ ጤና እና ስነ-ምግብ ላይ ሊያሳድር የሚችለውን ተፅዕኖ ለመከላከል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ሀይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር በጤና እና በስነ-ምግብ መጠበቅ ላይ ያለውን ሚና በተመለከተ የምርምር ጉባኤ የዘርፉ ተዋናዮች በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል። ዶክተር መሳይ ሀይሉ በመድረኩ እንደተናገሩት፤ ከተለያዩ የህብረተሰብ ጤና ፈተናዎች መካከል ከውሃ ጋር በተገናኘ የሚፈጠሩ የጤና ችግሮች እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን ለመሻገር እየወሰደቻቸው ያሉ የፖሊሲ እርምጃዎች ትልቅ ሚና አላቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን መትከሏ ተስማሚ የአካባቢ አየር ንብረት እንዲኖር አድርጓል ብለዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ አረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማበረታታት የወሰደቻቸው የፖሊሲ እርምጃዎች የአየር ብክለትን በመቆጣጠር የማኅበረሰብን ጤና ለመጠበቅና ስነ-ምግብን ለማሻሻል የራሳቸው አበርክቶ እንዳላቸው ገልጸዋል። ኢንስቲትዩቱ በአረንጓዴ ልማት ላይ የሚሰሩ ስራዎችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በማጥናት የደን ልማትና ንጹህ መጓጓዣ የመፍጠር እርምጃዎች ከአየር ንብረት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን የበሽታ ጫናዎች እንደሚቀንሱ፣ የአየር ጥራትን እንደሚያሻሽሉ እና የስነ-ምግብ ክትትልን እንዴት እንደሚያጠናክሩ በጥናት የማረጋገጥ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ኢንስቲትዩቱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚሰሩ ስራዎች በጤናው ዘርፍ ያላቸውን አበርክቶ በምርምር ስራዎች ለመፈተሽና በቀጣይ በሚሰሩ ተግባራት ላይ ከተለያዩ ተቋማት ጋር ያለውን የትብብር ስራ ለማጠናከር መድረኩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፈጠነ ተሾመ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ተቋሙ በመረጃ ላይ የተመሰረቱ የአየር ፀባይ ትንበያዎችን በመተንተንና በማደራጀት ለጤናው ዘርፍና ለልዩ ልዩ ጥቅሞች እንዲውሉ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተገናኙ መረጃዎችን በመለዋወጥ የማህበረሰብ ጤና እንዲጠበቅ ትብብሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ለበሽታ ክትትል፣ ለአደጋ ዝግጁነት እና ለቅድመ ማስጠንቀቂያ የሚረዱ የአየር ንብረት መረጃዎችን በወቅቱና በቀጥታ ለማድረስ ተግቶ ይሰራል ነው ያሉት።
የኢትዮጵያውያን ኅብር በውጤት የተገለጠበት - አረንጓዴ አሻራ
Sep 9, 2026 187
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ ባለፉት አሥርት ዓመታት የደን መመናመን፣ የአፈር መሸርሸር፣ የለም መሬት እየቀነሰ መምጣት እና ተደጋጋሚ ድርቅን ጨምሮ እጅግ አስቸጋሪና ተደራራቢ የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ይገጥሟት ነበር። ይህ የስነ-ምህዳር መዛባት በሚሊዮን የሚቆጠሩ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮችን ህይወትና የምግብ ዋስትና አደጋ ላይ ጥሎት ቆይቷል። በተለይም በቆላማ እና ከፊል አርብቶ አደር በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች የውሃ ምንጮች መድረቅ እና የግጦሽ መሬቶች መውደም ሰብአዊ ህይወቶችንና የቁም እንስሳትን ለአደጋ አጋልጧል። የብዝሃ ህይወት መመናመን ሌላኛው ፈተና ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን፣ ይህ የተፈጥሮ ሀብት መመናመን በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት ጎዳና ላይ ትልቅ ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል። ኢትዮጵያ ይሄን የአየር ንብረት ለውጥ በዘላቂነት ለመከላከል እና የተፈጥሮ ሀብትን ለመጠበቅ ከቃል ያለፈ የተግባር ስራ ከጀመረች ዓመታት ተቆጥረዋል። የዚህ ሀገራዊ ስራ አበይት መገለጫ ከሆኑ ብሔራዊ ኢኒሼቲቮች መካከል “አረንጓዴ አሻራ” ተጠቃሽና ግንባር ቀደም መርሃ ግብር ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የደን መመናመንን ለመግታትና ሥነ-ምህዳርን ለመመለስ የተጀመረ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ስራ ዛፍ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያውያን በአንድነትና በህብር በመቆም በጋራ የሰሩበት ታላቅ ህብረተሰባዊ አቅም የታየበት ማረጋገጫም ሆኗል። ሀገሪቱ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን ታላቁን የዓለም አቀፍ አየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ 32) በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እንድታስተናግድ መመረጧ፣ በአረንጓዴ ልማት ያሳየችው የህብርና የአንድነት ጉዞ ያስገኘው ትልቅ ዓለም አቀፋዊ ድል ነው። በአረንጓዴ አሻራ ስኬት ትልቁ መገለጫ የህዝቦች የጋራ ትብብር እና ተደጋግፎ መስራት መሆኑን በተግባር ለማሳየት ተችሏል። የኢትዮጵያ የደን ሽፋን በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 17.2 በመቶ በጥቂት ዓመታት ውስጥ ማለትም በ2017 ዓ.ም ወደ 23.6 በመቶ ማደግ ችሏል። እስካሁን ከ54 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በአንድነት በመሳተፍ ለአየር ንብረት ተጋላጭ የነበሩ አካባቢዎች አረንጓዴ ለብሰው እንዲለወጡ አድርገዋል። በብራዚል ቤለም በተካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን ኢትዮጵያን የኮፕ 32 አስተናጋጅ አድርጎ በሙሉ ድምፅ መምረጡ የህብር እና የአንድነት ውጤት ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬት የተለካው ችግኝ በመትከል ብቻ ሳይሆን፣ ህዝብና መንግስት በህብር ተክሎ የማሳደግና የመንከባከብ ባህልን በማዳበር ሲሆን የተተከሉ ችግኞች የመጽደቅ ምጣኔ ከ85 በመቶ በላይ ሆኗል። ይህ ሂደት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከአቮካዶ፣ ማንጎና ፓፓያ የመሳሰሉ የፍራፍሬ ችግኞች መተከል ጋር ተያይዞ የግብርና ምርታማነትን ያሳደገ ሲሆን፣ ለብዙ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል። መርሃ-ግብሩ ከደን ዛፍ ችግኝ ባለፈ የምግብ እና የከተማ ውበት መሰረት የሆኑትንም ያካተተ በመሆኑ ውጤቱን የላቀ አደርጎታል። የግብርና ምርታማነት እንዲጨምርም ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት የተደረገ የአካባቢ ጥበቃ ስራ ብቻ ሳይሆን፣ ሕዝቦች በአንድነትና በህብር ሲሰለፉ ሀገራቸውንና መልክዓ ምድራቸውን መቀየር እንደሚችሉ ለዓለም ያሳዩበት ታላቅ ማረጋገጫ ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ የትውልዱ ዳግማዊ ዓድዋ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ምልክት
Sep 7, 2026 281
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ መትከል ብቻ አይደለም፤ አካባቢን ለኑሮ ምቹና ማራኪ ገጽታ ማላበስ፣ የተፈጥሮን ሥነ-ምህዳር መጠበቅ፣ ለዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋም ጠጠር መጣል፣ ኢትዮጵያ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የሚገዳትና ለመፍትሔውም በግንባር ቀደምትነት የምትሳተፍ መሆኗን ማሳያ ጭምር እንጂ። አረንጓዴ ዐሻራ ለኢትዮጵያ ወንዞቿን በደለል ከመሞላት፣ አፈሯን ከመሸርሸር መታደግ፣ የዜጎቿን የምግብ ዋስትና የማረጋገጥና ምድሯን አረንጓዴ የማልበስ ኢኒሼቲቭ ነው። ከሰባት ዓመት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ኢኒሼቲቭ ሲያስጀምሩ፤ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቋቋም አይበገሬ ኢኮኖሚ መገንባት የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ አንዱ ሰበዝ እንደሆነ በመናገር ነበር። ኢትዮጵያ ዛሬ ለምግብነትና ለደን ልማት አገልግሎት፣ ለአካባቢ ውበትና መናፈሻ የሚውሉ በርካታ ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ታሪክ ሠርታለች። በአረንጓዴ ዐሻራ የደረቁ ሐይቆች አገግመዋል፤ በደለል የሚሞሉ ሐይቆችን መታደግ ተችሏል፤ የሚሸረሸረው ለም አፈርም ከመታጠብ ድኗል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አረንጓዴ ዐሻራ የተረጅነት ታሪክን በአዲስ ምዕራፍ በመተካት የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዞ ጅማሬ መሆኑን ገልጸዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ዜጎች በአካባቢያቸው የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ በማስቻል ለኢኮኖሚ ማንሰራራት መሠረት እየጣለ መጥቷል ብለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ብልፅግና ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ሀገራዊ ትልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የትውልዱ ዳግማዊ ዓድዋና የኢትዮጵያ የማንሰራራት ምልክት መሆኑን ገልጸዋል። ትውልዱ እንደ ትናንቱ ዓድዋ ሁሉ የዛሬውን አረንጓዴ ዐሻራ ከአባቶቹ የወረሰው የሀገር ማስቀጠያ ስንቅ በማድረግ በታሪክ ያወሳዋል ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን መሪነትና የተለየ ሚና የሚያጎላ የድል ችቦ መሆኑን ገልጸዋል። በአረንጓዴ ዐሻራ የተመዘገበው ውጤት በአፍሪካ አህጉር የወካይነት ሚና እንዲኖራት ማስቻሉን በማንሳት፤ ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ኩነቶችን ለማስተናገድ እምነት የሚጣልባት ሀገር ሆናለች ብለዋል። ይህም ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃና በአየር ንብረት ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት እንድትሰለፍ ማድረጉን ገልጸዋል። የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፤ የአረንጓዴ ዐሻራ በአካባቢ ጥበቃ ብቻ የተገደበ ሳይሆን ለግብርና ምርትና ምርታማነት ገንቢ ሚና አለው ብለዋል። በኢትዮጵያ የሰብል ምርት ዕምርታዊ ለውጥ እንዲያስመዘግብ በማስቻል በስንዴ ምርት ብቻ ከተረጂነት ወደ ትርፍ አምራችነት በመሸጋገር የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞ እያበሰረ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአቮካዶና በሌሎች የሆርቲካልቸር ምርቶች ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሪ እንድታገኝ አስችሏታል ብለዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርና ሌሎች የተቀናጁ የተፋሰስ ጥበቃ ሥራዎች በውሃ ሀብት ልማት በኩል ጉልህ ለውጥ ማስገኘታቸውን ገልጸዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ የሐይቆችን የደለል ክምችት በመቀነስ ብዙ ውሃ እንዲይዙ በማድረግ የግድቦችን ዕድሜ ማራዘም አስችሏል ብለዋል። የደረቁ ምንጮችና ሐይቆች እንዲያገግሙ አድርጓል ያሉት ሚኒስትሩ፤ የውሃና የተፈጥሮ ሀብትን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ማስቻሉን ገልጸዋል።
ጽዱ ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ በርካታ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Sep 7, 2026 148
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ):- ጽዱ ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ በርካታ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የፌዴራል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ ገለጹ። «ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ» በተሰኘው ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ማዕቀፍ የተዘጋጀና በአደገኛ ቆሻሻ አስተዳደር፣ በኤሌክትሮኒክስ ብክነት (e-waste) እንዲሁም በኬሚካሎች ደህንነቱ የተጠበቀ አያያዝና ማስወገድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ የፌዴራልና የክልል አካባቢ ጥበቃ ተቋማት ኃላፊዎች፣ የጤና ቢሮዎች ተወካዮች፣ የምርምርና የአካዳሚክ ተቋማት ተመራማሪዎች እንዲሁም በግል ዘርፍ የሚንቀሳቀሱ የቆሻሻ አስተዳደር ኦፕሬተሮች ተገኝተዋል። የፌዴራል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በሀገሪቱ «ጽዱ ኢትዮጵያን» በመፍጠር በኩል በርካታ አርዓያነት ያላቸው ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡ በዚህም የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ በከፍተኛ ሁኔታ መቻሉንና ለአካባቢ ጥበቃና ጽዳት ጥሩ ውጤት እየተገኘ መሆኑን አመልክተዋል። በቀጣይም የሚሰራውን ስራ በማጠናከር ጽዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ አመልክተዋል። ከዚህ ጋር በተያያዘም በአካባቢ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ አገልግሎት የጨረሱ ኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችና ሌሎች ቆሻሻዎችን ለመከላከል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ መንግስት ችግሩን ለመከላከል የሕግ ማዕቀፎችን፣ ደረጃዎችንና የሕግ ማስፈጸሚያ ሥርዓቶችን በማጠናከር በኩል የሚጠበቅበትን ሚና እየተወጣ መሆኑንም ምክትል ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል። በመሆኑም ችግሩን ይበልጥ ለመቅረፍ የሁሉም ርብርብ ወሳኝ መሆኑንና የመንግሥት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የምርምር ተቋማትና የሕብረተሰቡ ቅንጅታዊ አሠራር ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት ጠቁመዋል። በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የአካባቢ ተከባሪነትና ተፈጻሚነት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አዲሱ ጥበቡ በበኩላቸው አደገኛ ቆሻሻ ዓለም አቀፍ ትኩረት የተሰጠው ችግር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ቆሻሻዎችን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችል ሥርዓት ዘርግታ እየሰራች ትገኛለች ብለዋል። የፒዩር ኧርዝ የቴክኒካል ፕሮግራሚንግ ዳይሬክተር በረከት ተስፋዬ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ድርጅታቸው ከመንግሥት ጋር የተቀናጀ አሠራር ዘርግቶ እየሰራ መሆኑንና በቀጣይም ይህ የጋራ ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አፍሪካ በዓለም ፊት ቦታ ለማግኘት አትማጸንም ፤ ይልቁንም የሚገባትን ስፍራ በባለቤትነት እየያዘች ነው
Sep 9, 2026 101
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ):- አፍሪካ በዓለም ፊት ቦታ ለማግኘት አትማጸንም ፤ የሚገባትን ስፍራ እና ክብር በራሷ እያረጋገጠች ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ቀን ዛሬ እየተከበረ ይገኛል። የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ቀኑን በማስመልከት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት ቀን እ.አ.አ በ1999 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለመተካት ይፋዊ ውሳኔ የተላለፈበት የሰርጥ ድንጋጌ (Sirte Declaration) የሚታወስበት እንደሆነ ገልጸዋል። በዚያን ወቅት የአፍሪካ መሪዎች አህጉራዊ ትስስርን ለማፋጠን እና የአፍሪካን ድምጽ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ለማድረግ የአፍሪካ ህብረትን ለመመስረት ወሳኝ እና ታሪካዊ እርምጃ የወሰዱበት ምዕራፍ ነው ብለዋል። የዘንድሮው የአፍሪካ ህብረት ቀን ለአህጉሪቱ እጅግ ልዩ ትርጉም ባለው ወቅት ላይ እየተከበረ እንደሚገኝ አውስተዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ የአፍሪካን እውነተኛ ቁመና እና ትክክለኛ መጠን የሚያሳይ የዓለም ካርታ አጠቃቀምን የሚደግፍ፣ በአፍሪካ መሪነት የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ አፅድቋል። በቶጎ ሃሳብ አመንጪነትና በአፍሪካ ህብረት ድጋፍ እውን የሆነው ይህ እርምጃ ከቀላል የካርታ ማስተካከያ በላይ ትርጉም አለው ብለዋል ሊቀ መንበሩ። አፍሪካ በዓለም ፊት እንዴት እንደምትታይ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን እና አፍሪካ ራሷን የምትገመግምበትንና የምታሳይበትን ትርክት ራሷ መቅረጽ እንዳለባት አበክሮ የሚያስታውስ ነው። ይህ ውሳኔ አፍሪካ በዓለም ፊት በምን መልኩ መታየት እንዳለባት ከማሳየቱም በላይ፤ አፍሪካ ራሷን የምትመዝንበትንና እውነታዋን ለዓለም የምታሳይበትን ትርክት በራሷ መቅረጽ እንዳለባት በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን ነው ያነሱት። የአፍሪካ እጣ ፈንታ የሚወሰነው በአፍሪካውያን የራሳቸው እይታ ነው። አፍሪካን በእውነተኛ ቁመናዋ፣ኃይሏ እና አቅሟ የምንመለከትበት ጊዜ አሁን ነው ብለዋል። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር አያይዘውም ካርታውን የማስተካከል እርምጃ አፍሪካ ወደ ላቀ የጋራ ራዕይ የምታደርገው አህጉራዊ ጉዞ አካል መሆኑን አንስተዋል። ይህም በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠና (AfCFTA) አማካኝነት የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከርን፣ ሰላም እና ፀጥታን ማረጋገጥን፣ ዘላቂ ልማትን እውን ማድረግን እና በዓለም አቀፍ ውሳኔ ሰጪ አካላት ውስጥ የአፍሪካን ተሳትፎ ማሳደግን እንደሚያካትት በዝርዝር አስረድተዋል። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የተሳሰረች፣ የበለጸገች እና ሰላማዊት አፍሪካን ለመገንባት የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ሰላም እና ፀጥታን ማረጋገጥ፣ የኢኮኖሚ ትስስርን በማፋጠን እና የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ተሰሚነት መጨመር የአፍሪካ ህብረት ቀዳሚ ትኩረቶች ናቸው ብለዋል። አፍሪካ በዓለም ፊት እውቅና ለማግኘት አትለምንም፤ ይልቁንስ በዓለም አቀፍ መድረክ የሷ የሆነውን ትክክለኛ ስፍራ በራሷ ባለቤትነት እየያዘች ነው። አሁን የሚጠበቅብን ይህንን ጠንካራ እምነት ወደ ህብረት፣ ሀብትና ብልጽግና፣ ሰላም እና ተደማጭነት መለወጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ሊቀመንበሩ አፍሪካ የምታስመዘግበው እድገት በዓለም አቀፍ መድረኮች በሚኖራት ውክልና ብቻ ሳይሆን፣ በዜጎቿ ላይ የኑሮ ጥራት መሻሻል ጭምር መለካት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል። በዚህም መሰረት የአፍሪካ ህብረት የ2026 ዓመት ትኩረቱን በዘላቂ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አገልግሎት ላይ ማድረጉ፣ ህብረቱ አህጉራዊ ራዕዮችን ከዕለት ተዕለት የዜጎች ህይወት ጋር ለማያያዝ ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አመልክተዋል። በአፍሪካ ህብረት ቀን አከባበር አባል ሀገራት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የአፍሪካ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ሴቶች እና ወጣቶች ተባብረው ይበልጥ የተሳሰረች፣ በራሷ አቅም የምትተማመን እና የራሷን እጣ ፈንታ በራሷ መወሰን የምትችል አፍሪካን እንዲገነቡ ሊቀመንበሩ ጥሪ አቅርበዋል። የምንፈልጋት አፍሪካ የሚለውን አህጉራዊ ራዕይ እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ እና የሰርት ድንጋጌ ለቀጣዩ የአፍሪካ ትውልድ ዘላቂ የትምህርት እና የዕድገት መሰረት ሆኖ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የነገዋ አፍሪካ በካርታ ላይ ብቻ የተሻለ ውክልና ያላት ብቻ ሳትሆን፤ በዓለም አቀፍ መድረክ ሉዓላዊነቷ የጸና፣ ጠንካራ ውስጣዊ አንድነት ያላት፣ ለህዝቦቿም ዘላቂ ብልጽግናን የምታጎናጽፍ አህጉር መሆን ይኖርባታል ነው ያሉት። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር ለመላው አፍሪካውያን እና በውጭ ሀገር ለሚገኙ የአፍሪካ ዳያስፖራዎች ሰላማዊ እና የትብብር መንፈስ የተሞላበት የአፍሪካ ህብረት ቀን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ አጋርነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Sep 4, 2026 433
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 29/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን እና ሁሉን አቀፍ ትብብራቸውን የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ውይይቱ በአፍሪካ ህብረትና አሜሪካ መካከል ያለውን ለረጅም ጊዜ የቆየ አጋርነት ማጠናከር እና በአህጉሪቱ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር የአፍሪካና አሜሪካን ትብብር ታሪካዊ መሆኑን አውስተው በህብረቱ፣ በአባል ሀገራት እና በአሜሪካ መካከል የሁለቱንም ወገኖች ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ ጠንካራ አጋርነት መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል። በምስራቅ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሱዳን እየተደረጉ ላሉ አፍሪካ መር የሰላም ጥረቶች አሜሪካ እያደረገች ላለው ገንቢ አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያ በበኩላቸው አፍሪካ አሜሪካ ቀዳሚ ትኩረት የምትሰጣት አህጉር እንደሆነች ገልጸዋል። የጋራ ፍላጎቶችንና ግቦችን ከህብረቱ ኮሚሽንና ከአባል ሀገራት ጋር በመሆን ለማሳካት ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በዲፕሎማሲ፣ እንዲሁም በሰላምና ጸጥታ ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባም አመልክተዋል። በውይይቱ ላይ በሱዳን ጉዳይ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የሰብአዊ እርዳታ ያለ ገደብ እንዲገባ እና በሲቪሎች የሚመራ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመር አጽንዖት ተሰጥቷል። በአፍሪካ ባለቤትነት የሚመሩ የሰላም ጥረቶች እና አሜሪካ የምትደግፋቸው የሰላም ሂደቶች በተቀናጀ መልኩ ለመተግበር ከስምምነት ላይ ተደርሷል። በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመሰረተ ልማት እና በሰላም መስኮች የሁለቱን ወገኖች ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ የትብብር መስኮች ተገምግመዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ህብረትና በአሜሪካ ስትራቴጂክ ኢንቨስትመንት ማዕቀፍ ውስጥ የተደረጉ ስምምነቶችን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። በሊቢያ ጉዳይ ዘላቂ የፖለቲካ መፍትሄ ማግኘት እንደሚያስፈልግም ተነስቷል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር እና ረዳት ሚኒስትሩ የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና የትብብር አድማሱን ለማስፋት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 1740
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 1393
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች። ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
ሐተታዎች
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦች የመቻል ተምሳሌት
Sep 9, 2026 100
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦች የመቻል ተምሳሌት መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም የኢትዮጵያውያን የጋራ ቃል ኪዳን የታሰረባት ታሪካዊ ክስተት ናት። ዕለቷም የዓባይን የሺሕ ዘመናት ገደብ የሌለው ጉዞ በጉባ ተራሮች ግርጌ ልጓም ለማበጀት የታሰረች ቀለበት ሆና ተመዝግባለች። ኢትዮጵያውያን ቃል ኪዳናቸውን ባሰሩ ማግስት የግብፅና ሌሎች ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጩኸትና የጥፋት ሴራ በግልጽ መታየት ጀመረ። በተለይም ግብፅ ኢትዮጵያ ውስጣዊ መረጋጋት እንዳይኖራት የውስጥ ታጣቂዎችን ከመደገፍ ጀምሮ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በራፍ ጭምር የሀሰት ክሶችን እስከማሰማት የደረሰ የሺሕ ዘመናት ዓባይን በብቸኝነት የመጠቀም አባዜዋን አንጸባርቃለች። ትብብርን ከፅናት አሰናስለው የቀጠሉት ኢትዮጵያውያን ለአሥራ አራት ዓመታት የታላቁ ሕዳሴ ግድብን የማደናቀፍ የታሪካዊ ጠላቶችን ሴራ በጋራ በመመከት ለፍጻሜ አብቅተውታል። የሀገርን ሉዓላዊነት በጽናት የማስከበር የአርበኝነት ተጋድሎን ከዓድዋ ጀግኖች የወረስን እኛ ኢትዮጵያውያን በጉባ ተራሮች ግርጌ በደም፣ በላብ፣ በዕንባና በውኃ ጠብታ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን በዓባይ ላይ አንጸናል። ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የአዲስ ዓመት ዋዜማም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በማጠናቀቅ ለፍጻሜ በማድረስ አብስሯል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሺሕ ዘመናት የልማት ጥማትን በማርካት የብልፅግና ፍኖት ብስራት ሆኗል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ለሌላ የልማት ዕቅድ ወጋገን የፈነጠቀ የንጋት ሐይቅ ፈጥሯል። ግድቡ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝቦቿ ትብብር ብቻ ያለ አንዳች የውጭ ድጋፍና ብድር ለፍጻሜ መብቃቱም ለአፍሪካውያን የመቻል ትዕምርት ሆኗል። በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ብስራት በጉባ ተራሮች ግርጌ የከተሙ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት መሪዎች የመሰከሩት ጥሬ ሐቅም ይህ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምረቃው ዕለት እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የጥቁር ሕዝቦችን የታሪክ ክብር ያደሰና ለአፍሪካውያን የመቻል ውጤት ነው። በወቅቱም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጎህ ያበሰረ፣ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርና የጋራ ዕድገት መንገድ የጠረገ ፓን-አፍሪካኒዝም ፕሮጀክት መሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ አፍሪካውያን አንጡራ ሀብታቸውን በራሳቸው አቅምና ጥረት በማልማት ታላላቅ የልማት ገድሎችን መፈጸም እንደሚችሉ ያመላከተ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የኩራት ምንጭ መሆኑንም ጠቁመዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር እና የክብር እንግዳ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ የታዳሽ ኃይል ሽግግርን በማፋጠን የአፍሪካውያንን የጋራ ምኞት የሚያሳካ ህያው ምልክት ነው ማለታቸው ይታወሳል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅና ለምረቃ መብቃትም የኢትዮጵያውያንን ለአንድ ሀገራዊ የልማት ርዕይ በጋራ የመቆም ውጤታማነትን በተግባር ለዓለም የገለጠ ፓን-አፍሪካኒዝም ፕሮጀክት መሆኑን መስክረዋል። በዚሁ ወቅት የተገኙት የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጌሌ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዘመናዊው ዓለም የአፍሪካውያን የኩራት ምንጭ የሆነ የልማት ድል መሆኑንና መላውን ዓለም ያስደነቀ የኢትዮጵያ ስኬትና የወዳጆቿ የጋራ ሀብት ነው። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ብሔራዊ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን አስደማሚ የፓን-አፍሪካኒዝም መግለጫ ፕሮጀክት ነው ያሉት ደግሞ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ የታደሙት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ናቸው። የኢትዮጵያውያን ብሔራዊ ፕሮጀክት የሆነው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት አፍሪካውያን በተባበረ ክንድ አቅማቸውን በመጠቀም የራሳቸውን ዕድል በራሳቸው መወሰን እንደሚችሉ ትምህርት ያስተላለፈ ነው ሲሉም መግለጻቸው ይታወሳል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የምህንድስና ልህቀትም አህጉሪቱ ለብልፅግናዋ የሚረዱና ሁለንተናዊ ለውጥ የሚያመጡ ሁነኛ የልማት ፕሮጀክቶችን በራሷ አቅም የመገንባት ብቃት እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ላይ የተገኙት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ እንደተናገሩት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አህጉራዊ ትብብርና ግንኙነትን የሚያጠናክር የወንድማማችነት ምልክት ነው። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁላችንንም ተጠቃሚ የሚያደርግ የጋራ ጉዳያችን ነው በዚህም ዕድለኞች ነን ሲሉ መግለጻቸውም ይታወሳል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ "ለእኛ እንደ አንድ ፕሮጀክት ሳይሆን ሀላፊነትን የምንጋራበት ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ አፍሪካውያን ከተባበርን ስኬቶችን ማስመዝገብ እንደምንችል ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። የላይኛውና የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት መበልጸግ የሚችሉት በጋራ እንደ አንድ ማህበረሰብ በመስራት ነው። ውሃና ሌሎች ተፈጥሯዊ ሀብቶች በድንበር የተወሰኑ ሳይሆኑ የወደፊት እጣ ፈንታችንን የሚወስኑ ናቸው ብለዋል። የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት በበኩላችው እንደሚሉት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአንድነት እና የመስዋዕትነት ምልክት ነው። ግድቡ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን የአንድነትና የመስዋዕትነት ምልክት ነው፡፡ የግድቡ ግንባታ እውን መሆን ህዝብ ከተባበረ እና ለአንድ ዓላማ በአንድነት ከቆመ ምን መስራት እንደሚችል ማሳያ መሆኑን ነው ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህም ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የኩራት ምንጭ ነው ማለታቸው ይታወሳል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ግድቡ የኃይል ፍላጎትን ከማሳካት ባለፈ ለልጆቻችን የምንመኘውን የበለጸገ ሀገርና አህጉር ለማስረከብ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ይህ በታሪክ ድርሳናት ሰፊውን ድርሻ የሚይዘው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት የኢትዮጵያዊያን የቃል ኪዳናቸው ማህተም ሆኖ ለዘላለም ይኖራል።
የፀጥታና ደህንነት ተቋማት በመጠናከራቸው ኢትዮጵያን የማትበገርና የጸናች ሀገር አድርጓታል
Sep 8, 2026 225
የፀጥታና ደህንነት ተቋማት በመጠናከራቸው ኢትዮጵያን የማትበገርና የጸናች ሀገር አድርጓታል ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን፣ ሰላሟንና የሕዝቦቿን ደህንነት ለማስጠበቅ ባለፉት ዓመታት በጸጥታና ደህንነት ዘርፍ በተቋማዊ አደረጃጀት፣ በሕግ፣ በሙያዊ አቅም ግንባታ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በተቀናጀ አሠራር ያካሄደቻቸው ሪፎርሞች የጸጥታ አቅሟን እንድታሳድግ አስችለዋል። በዚህም የፖሊስና የመረጃ ተቋማት የሚመሩበት የሕግ ማዕቀፍና ተቋማዊ አደረጃጀቶችን ከማጠናከር ባሻገር፣ ተቋማቱ የዘመኑን የጸጥታ ተግዳሮቶች መመከት የሚያስችላቸውን አቅም እንዲገነቡ ተደርጓል። በመከላከያ ዘርፍም የሠራዊቱን አደረጃጀትና የማድረግ አቅም ማጎልበት፣ የቴክኖሎጂ አቅሙን ማጠናከር የሪፎርሙ የትኩረት አቅጣጫዎች ነበሩ። በዚህም የምድር ጦርን ጨምሮ የአየር ኃይልና የባሕር ኃይል አቅምን ማጠናከር እንዲሁም ከዘመናዊ የሰራዊት አሠራር ጋር የሚሄድ የወታደራዊ አቅም መገንባት በዚሁ አቅጣጫ ተካትቷል። በቅርቡ በሃዋሳ በተካሄደ የኮማንዶ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ ኢትዮጵያ የሀገሪቱን ደህንነት ከማስጠበቅ ባለፈ በቀጣናውና በአፍሪካ ሰላምና ብልጽግና ላይ አስተዋፅዖ ማድረግ የሚችል በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ኤሊት የጦር ኃይል ለመገንባት እየሠራች ነው። በምድርና በአየር የነበረውን ወታደራዊ ሥልጠና ወደ ባሕር ማስፋፋትን ጨምሮ፣ የጦር ኃይሉን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማጠናከርና የተለያዩ የውጊያ አቅሞችን ማሳደግ የሠራዊቱን ዘመናዊነት ለማረጋገጥ ከተወሰዱ አቅጣጫዎች መካከል መሆናቸውን መጠቆማቸው ይታወሳል። በተመሳሳይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ በ45ኛው የፅናት ኮርስ የኮማንዶ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ እንዳሉት፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የተጠናከረ ወታደራዊ አቅም እንዲኖረው ተሰርቷል። የቴክኖሎጂ ግኝቶችን የታጠቅንበት ዘመን ላይ ነን ያሉት ፊልድ ማርሻሉ፣ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ውስጥና የውጭ ጠላቶች እንደማይችሏት ገልጸዋል። የጸጥታ ተቋማት በተናጠል ከመሥራት ይልቅ በቅንጅት እንዲሠሩ ማድረግም በሪፎርሙ የተሰጠው ትኩረት ሌላው አቅጣጫ ነው። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፣ የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮችና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች ሀገራዊ የጋራ የፀጥታ መድረክ ላይ እንደገለጹት፣ የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ የጸጥታ ተቋማት በጋራ በማቀድ፣ በመቀናጀትና ልምድ በመለዋወጥ የጋራ የጸጥታ ተልዕኮዎችን የሚያከናውኑበት አሠራር ተጠናክሯል። ይህ የተቀናጀ አሠራር በተለያዩ ብሔራዊ ዝግጅቶችና የሀገራዊ ጸጥታ ተልዕኮዎች ወቅት የተቋማትን የጋራ አቅም ለመጠቀም መሠረት መሆኑ በቀደመ ማብራሪያዎች ጠቁመዋል። የሳይበር ደህንነት የሀገራዊ ደህንነት አካል እየሆነ መምጣቱ የሪፎርሙ አንድ አካል እንዲሆን ተደርጓል። በዚህ ረገድ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ አምስተኛው ዙር ብሔራዊ የሳይበር ታለንት የሰመር ካምፕ ማስጀመሪያ መርሃግብር ላይ እንደገለጹት፤ አስተዳደሩ ተቋማዊ አቅሙን በማሳደግ ወሳኝ የመረጃ መሠረተ ልማቶችን ከሳይበር ጥቃቶች ለመጠበቅ የሰው ኃይል ልማት፣ የዝግጁነት አቅምና የተቋማት ትብብርን ማጠናከር ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል። የሳይበር ደህንነት የሀገሪቱን ዲጂታል ሽግግር ለማረጋገጥ ወሳኝ በመሆኑ በዘርፉ ብቁ የሰው ኃይል ማፍራትና የተቋማትን ዝግጁነት ማጠናከር ቀዳሚ ትኩረት ነው ብለዋል። በአጠቃላይ በሀገሪቱ የጸጥታና ደህንነት ዘርፉ የተከናወኑት ሪፎርሞች የጸጥታና ደህንነት ሥርዓቱን በተቋማዊ አደረጃጀት፣ በሙያዊ ብቃት፣ በቴክኖሎጂና በቅንጅታዊ አሠራር ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፣ ይህም ሀገሪቱ የራሷን የጸጥታ አቅም በማሳደግ ሉዓላዊነቷን፣ ሰላሟንና ብሔራዊ ጥቅሟን በበለጠ አቅም ለማስጠበቅ ያላትን ብቃት አጠናክሯል።
በልጆቿ ፀንታ የኖረች ሀገር
Sep 8, 2026 378
በብርሀኑ ፍቃዱ (ሰቆጣ ኢዜአ) የውጪ ወራሪን በጀግኖች አባቶቻችን ክቡር መስዋዕትነትና በጸና ተጋድሎ በማክሸፍ፣ ኢትዮጵያን በትውልድ ቅብብሎሽ አጽንቶ አሁን ላለንበት ማድረስ ተችሏል። ለአብነትም የጣሊያን ወራሪ ኃይል በጥንት አባቶቻችን ተጋድሎ ሽንፈትን ተከናንቦ መመለሱ ለኢትዮጵያዊያን ድልና ለመላው ጥቁር ህዝብ የነፃነት ፋኖስ ሆኖ ሲዘከር ይኖራል። "የአይቻልም" መንፈስን በ"ይቻላል" ለውጠው ያሳዩት እነዚህ ጀግኖች፣ ለጥቁር ህዝቦች የነፃነት ጮራ የፈነጠቁ፣ እኩልነትን ያበሰሩ፣ የሀገር ፍቅርና ጽናትን ለልጅ ልጆቻቸው ያወረሱ እንዲሁም ታሪክን በወርቅ ቀለም የጻፉ ናቸው። የዛሬው ባለታሪኮቻችን ሻለቃ ባሻ ሞገስ የማነብርሃን እና መቶ አለቃ አበባው ገብረ እግዚአብሔር ለሀገራቸው ሉዓላዊነት መከበር በጽናት ታግለው ያሳለፉትን የተጋድሎ ታሪክ «የጽናት ቀን»ን ምክንያት በማድረግ እንደሚከተለው እናስቃኛችኋለን። በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በሰቆጣ ወረዳ «ቃፋ ሚካኤል» በተባለ መንደር ነዋሪ የሆኑ ሻለቃ ባሻ ሞገስ የማነብርሃን፣ ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ ለ22 ዓመታት ክቡር በሆነው የውትድርና ሙያ ሀገራቸውን አገልግለዋል። "ጀግንነትን፣ አሸናፊነትን እና ለሀገር አንድነት መስዋዕት መክፈልን ከአባቴ ከሻለቃ የማነብርሃን የወረስኩት አኩሪ ታሪክ በመሆኑ፣ እኔም ለሀገሬ ክብር በጽናት ተዋድቄያለሁ" ሲሉ ይገልጻሉ። የውትድርና ሕይወታቸውን በቀብሪ ደሃር ማሰልጠኛ ማዕከል የጀመሩት ሻለቃ ባሻ ሞገስ፤ በዳሎል፣ ምፅዋ፣ ከረን፣ ሙሳቤት፣ ቃሮራ፣ አፋበት፣ ናቅፋ እና በሌሎች የኤርትራ ቆላማና ደጋማ አካባቢዎች የተሰጣቸውን ግዳጅ በጽናት ተወጥተዋል። "የወጣትነት እድሜዬን ክቡር የሆነውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት በመቀላቀል ሀገር የሰጠችኝን ግዳጅ በጽናት ተወጥቻለሁ" ያሉት ሻለቃ ባሻ ሞገስ፤ ሀገርን በውትድርና የማገልገል እድል ማግኘት ታላቅ ዕድልና ክብር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያን የመሰለች ጥንታዊት ሀገር ሉዓላዊነቷ፣ አንድነቷና ክብሯ እንዲጠበቅ አባቶቻችንም ሆኑ እኛ ዋጋ ከፍለናል፤ የአሁኑ ትውልድም ሉዓላዊነቷን አጽንቶ ለመዝለቅ ወቅቱ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዘብ መቆም አለበት ሲሉ ይመክራሉ። አሁን ያለው የሀገር መከላከያ ሠራዊት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በሰው ኃይል አቅምና ትጥቅ፣ ከሳይበር እስከ መካናይዝድ ልቆ የተደራጀ በመሆኑ ከኢትዮጵያ አልፎ ለቀጠናው ዘብ የሚሆን አስተማማኝ ኃይል መሆኑን እያየን ነው ብለዋል። "ሀገራችን የባሕር በር አልባ መሆኗ ያስቆጨኛል፤ ዕድሜ ልኬን ለሀገሬ ዘብ ብቆም ምኞቴ ነው" ያሉት ሻለቃ ባሻ ሞገስ፤ ወጣቱ ትውልድ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የተጀመረውን ተግባር በሰላማዊ መንገድ ለማሳካት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ መቶ አለቃ አበባው ገብረ እግዚአብሔር በበኩላቸው፤ «ታላቋን ሶማሊያ» ለመመስረት በሚል በጦር የሰከረው የዚያድ ባሬ መንግሥት በእብሪት ተነሳስቶ ሀገራችንን በወረረበት ወቅት በ18 ዓመታቸው የቀድሞውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት መቀላቀላቸውን ያወሳሉ። "ወላጅ አባቴ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የቀድሞ አባል ነበር" ያሉት መቶ አለቃ አበባው፤ እሳቸውና ታናሽ ወንድማቸው የአባታቸውን አሻራ በመከተል የመከላከያ ሠራዊቱን መቀላቀላቸውን ተናግረዋል። የ10ኛ፣ 19ኛ፣ እና 82ኛ ልዩ ኮማንዶ ክፍለ ጦሮች አባል በመሆን በሕክምና ሙያቸው ሠራዊቱን ለ12 ዓመታት ማገልገላቸውን ጠቁመው፤ ውትድርና ጽናትን፣ የሀገር ፍቅርን እና ከራስ በፊት ለወገን መስዋዕት መሆንን የሚጠይቅ የተከበረ ሙያ መሆኑን ገልጸዋል። ከሰራዊት አባልነት ከተገለሉም በኋላ ባካበቱት የሕክምና ሙያ በሰቆጣ ጤና ጣቢያና በተፈራ ኃይሉ ሆስፒታል ተቀጥረው ህዝባቸውን ያገለገሉ ሲሆን፣ የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ በመሆንም ሰርተዋል። "ለዘመናት ያዘንኩበት የባሕር በር ጉዳይ አሁን ላይ የትውልዱና የመንግሥት አጀንዳ ሆኖ መነሳቱ አስደስቶኛል" ያሉት መቶ አለቃ አበባው፤ ይህም የሀገራችንን የቀደመ ገናናነት የሚመልስ በመሆኑ ለስኬቱ በአንድነት መሰለፍ ይገባል ብለዋል። የአሸናፊነትና የጀግንነት ወኔ ከጥንት ጀምሮ ያለና የሚቀጥል መሆኑን አሁን ላይ የመከላከያ ሠራዊት ዘመኑን የዋጀ አደረጃጀትና የቴክኖሎጂ አቅም በማየት መገንዘብ ይቻላል ብለዋል። ወጣቱ ትውልድ ጸንታ የተከበረች ሀገሩን በአንድነትና በፍቅር ሉዓላዊነቷን ጠብቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንዳለበት መክረዋል።
የስኬት መገለጫና የውጤት ማሳያዎች
Aug 28, 2026 584
አዲስ አበባ ነሀሴ 22/2018 (ኢዜአ) የስኬት መገለጫና የውጤት ማሳያዎች በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብና የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (Homegrown Economic Reform) እቅዶችን በመተግበር በበርካታ ዘርፎች መሠረታዊ ለውጦችን እና ስኬቶችን ማስመዝገብ ተችሏል። በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጂታል (አይሲቲ)፣ በማዕድን እና በቱሪዝም ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብታዊ አቅም ከማሳደግ ባሻገር የወደፊት ዘላቂ እድገት መሠረት ያኖሩ መሆኑን መናገር ይቻላል። በመሆኑም በአምስቱ ዋና ዋና ሴክተሮች የመጡ ውጤቶችና የተመዘገቡ ስኬቶችን በወፍ በረር እንቃኛለን። 1. በግብርና ዘርፍ የስንዴ ምርትና የውጭ ኤክስፖርት: የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መስፋፋት ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሰረት አስቀምጧል። ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የስንዴ ምርትን ወደ ውጭ ሀገር መላክ የቻለችበትን እመርታዊ ስኬትም አሳይቶናል። የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭን በመተግበር በወተት፣ በእንቁላል፣ በዶሮና የማር ምርት እንዲሁም በአትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ሩዝና ሻይ ልማትም ባለፉት አምስት አመታት እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል። አርሶ አደሩ የመሬትና የውሃ ሀብቶችን አቃፊ በሆነ መንገድ በመጠቀም በዓመት ሁለትና ሶስት ጊዜ ማምረት የሚችልበት አሰራር ተዘርግቷል። በዚህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ሁነኛ የገቢ ምንጭ የሆነበትን እድል ፈጥሯል። ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የመቻል አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል። በተለይም ደግሞ የቡና ምርታማነትና ጥራት በማደጉ ምክንያት በኤክስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማገኘት ተችሏል። በዘርፉ በቀጣይም የግብርናውን ዘርፍ ይበልጥ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በሜካናይዜሽን በማስደገፍ ምርታማነትን የማሳደግ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። የመስኖ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት የዝናብ ጥገኝነትን ለመቀነስ መጣር እንዲሁም የግብርና ምርቶችን ጥራት በማሻሻልና በማቀነባበር ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ዋጋ ማሳደግ ተገቢ ይሆናል። 2. የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሀገራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ንቅናቄ በመፍጠር ቀደም ሲል ተቆልፈው የነበሩና በዝቅተኛ አቅምያመርቱ የነበሩ ፋብሪካዎች ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ ተደርጓል። የሀገር ውስጥ የምርት ፍላጎትን በመሸፈን ለውጭ ሀገር ምርቶች ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪም መቀነስ አስችሏል። ለሀገር ውስጥና ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ የህግና የአሰራር ሁኔታዎችን በመፍጠር በርካታ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ተችሏል። ከተገነቡት የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ፓርኮች (IAIPs) ጋር አርሶ አደሩን በማስሳሰር የግብአትና የምርት ትስስር እንዲጠናከር ተደርጓል። የአምራች ዘርፉ መስፋፋት ለብዙ ሺህ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች የሥራ እድል መፍጠር የታቸለበት ሆኗል። በቀጣይም የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በኃይል፣ በሎጂስቲክስና በግብአት አቅርቦት ሙሉ በሙሉ በመደገፍ ኤክስፖርትን ማሳደግ። የአምራች ኢንዱስትሪዎች 80% እና ከዚያ በላይ የሀገር ውስጥ ጥሬ ዕቃዎችን እንዲጠቀሙ ማበረታታት፣ በህዝብና በግል አጋርነት (PPP) አማካኝነት በትልልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ላይ የግሉን ዘርፍ አሳትፎ ማስፋፋት ትኩረት የሚደረግበት ይሆናል። 3. የዲጂታል (አይሲቲ) ዘርፍ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ስልት ስኬቶችን በማስቀጠል ወደ "ዲጂታል 2030" እቅድ መሸጋገር ተችሏል። በ"መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በሌሎች ፖርታሎች አማካኝነት ህዝባዊ አገልግሎቶችን በበይነ-መረብ (Online) የመስጠት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የዜጎችን መረጃ ማዕከላዊ የሚያደርግና ለፋይናንስ እንዲሁም ለሌሎች አገልግሎቶች መሠረት የሆነውን የፋይዳ መታወቂያ ፕሮጀክት በላቀ መልኩ ማሳካት ተችሏል። የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን የኮደር ስልጠናም የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ ታላቅ ሀገራዊ የስልጠና መርሃ ግብር ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።የዲጂታል አገልግሎቶች መዘርጋታቸው የፊት ለፊት ግንኙነትን በመቀነስ ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን በመከላከል የኢንቨስትመንት ምህዳሩን አሳልጧል። የቴሌኮም ዘርፍ ውድድር: የቴሌኮም ዘርፉን ክፍት ማድረግን ተከትሎ የኢንተርኔትና የኔትወርክ ተዳራሽነትንና ጥራትን በየገጠሩ የማስፋት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቶችን እና የባንክ አገልግሎቶችን ይበልጥ ዘመናዊና የተቀናጁ ማድረግም አስፈላጊ ይሆናል። የሀገሪቱን የዲጂታል መሠረተ ልማት ከሳይበር ጥቃቶች የመጠበቅ አቅምን ማጠናከር። 4. የማዕድን ዘርፍ በዘርፉ ይስተዋል የነበረውን ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ በመግታት ህጋዊ አሰራርና ቁጥጥር እንዲሰፍን ተደርጓል። የህግና መመሪያዎች ማሻሻያ በማድረግ የማዕድን ዘርፉን ለውጭና ሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ማራኪ የሚያደርጉ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ተደርገዋል። የወርቅ፣ የከሰል ድንጋይ፣ የሲሚንቶ ግብአቶችና የከበሩ ድንጋዮች ምርትን በማሳደግ ዘርፉ የሀገሪቱ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ እንዲሆን ተሰርቷል። በተለይም የከሰል ድንጋይ ምርትን በሀገር ውስጥ አምርቶ በመተካት ለፋብሪካዎች ግብአት ማቅረብ ተችሏል። 5. የቱሪዝም ዘርፍ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር)አነሳሽነት የተጀመሩት "ገበታ ለሸገር"፣ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች በመላ ሀገሪቱ በርካታ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን መገንባት ተችሏል። በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች የተከናወኑ የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበትና ለኑሮ ምቹነት ከመጨመራቸው ባሻገር ለከተማ ቱሪዝም ትልቅ እድል ፈጥረዋል። አዲስ አበባ በርካታ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችንና ኮንፈረንሶችን ባካሄደችበት የዲፕሎማሲና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷን አጠናክራለች። የሀገሪቱን ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች የመጠበቅ፣ የማደስና ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራዎች በስፋት ተከናውነዋል። በድምሩ ባለፉት አምስት ዓመታት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጂታል፣ በማዕድን እና በቱሪዝም ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች ሀገሪቷን ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ምዕራፍ ማሸጋገር አስችለዋል። በመሆኑም እነዚህን ስኬቶች አጠናክሮ ለማስቀጠል የታቀዱትን የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች በተቀናጀ መልኩ መተግበር፣ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ እና የግሉን ዘርፍ አሳታፊነት ማሳደግ በቀጣይ አዲስ የሚመሰረተው መንግስት ዋነኛ የቤት ስራ ይሆናል።
ትንታኔዎች
የስንዴ አብዮት፦ የኢትዮጵያ ማንሰራራት አብነት
Sep 6, 2026 528
ኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ107 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ነው። ይህንን ፍላጎት ለማሟላት ለዓመታት ከ700 ሚሊዮን ዶላር እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ውድ የውጭ ምንዛሬ ለስንዴ ግዢ ስታወጣ ቆይታለች። ከዚህ ቀደም ሀገሪቱ ከዓመታዊ ፍላጎቷ መሸፈን የምትችለው ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ብቻ ሲሆን፣ ቀሪውን በውጭ ግዢ ትሸፍን ነበር። በተለይም የዩክሬንና የሩሲያ ጦርነት በዓለም አቀፍ ደረጃ 30 በመቶ የሚሆነውን የስንዴ አቅርቦት በማወኩ ኢትዮጵያ ከባድ የአቅርቦት ፈተና ውስጥ እንድትገባ አድርጓት ነበር። ይህንን የረጅም ጊዜ ተግዳሮት በዘላቂነት ለመቅረፍ መንግሥት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በስፋት በመተግበር፣አሲዳማ መሬቶችን በኖራ በማከም እና ረግረጋማ ቦታዎችን በቴክኖሎጂ በማድረቅ ታሪካዊ ለውጥ ለማምጣት እርምጃዎችን ወስዷል። በኩታ ገጠም እርሻና በዘመናዊ ማሽነሪዎች አጠቃቀም የታጀበው ይህ የልማት አብዮት ፍሬ አፍርቶ፣ ኢትዮጵያ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ከውጭ የምታስገባውን የንግድ ስንዴ ሙሉ በሙሉ አቁማለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስንዴ ልማት የተመዘገበው ስኬት ከውጭ ማስገባትን ማቆም ላይ ብቻ ሳይወሰን፣ ሀገሪቱ ወደ ውጭ መላክ (ኤክስፖርት ማድረግ) የሚያስችል አቅም እንዳላት ያሳየ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም መሠረት የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን በይፋ የስንዴ ኤክስፖርት የተጀመረ ሲሆን፣ ለዚህ ስኬታማነት የተለያዩ ክልሎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚና የኤክስፖርት ኮሚቴ ሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ፍጆታዋን ሸፍና 32 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም እንዳላት አረጋግጦ፣የ2.9 ሚሊዮን ኩንታል የውል ስምምነቶች ከረድኤትና ከሀገር ውስጥ ድርጅቶች ጋር ተፈራርሟል። ከሀገር ውስጥ አቅርቦት ባሻገር ኢትዮጵያ በ2015 ዓ.ም ለኬንያ ስንዴ ለመላክ ስምምነት የፈረመች ሲሆን፣ ጅቡቲም ከኢትዮጵያ ስንዴ መግዛት እንደምትፈልግ ገልጻ ከኢትዮጵያ የስንዴ ልማት ብዙ ተሞክሮ እንደምትወስድ አመላክታለች። የአፍሪካ ልማት ባንክ ስንዴ ከውጭ እንደማታስገባ እና ምርቷን ለጎረቤት ሀገራት ማስተላለፍ መጀመሯን በማድነቅ ለአህጉሪቱ እንደ ትልቅ የዕድገት ተሞክሮ አቅርቧል። የአሜሪካ የውጭ ግብርና ቢሮ ሪፖርቶችም በኢትዮጵያ የስንዴ ምርት ዘርፍ ትልቅ እመርታ እያሳየ መምጣቱን ጠቅሰው፣መንግሥት የመስኖ ልማትና የግብርና ኤክስቴንሽን ድጋፍ በማጠናከሩ ሀገሪቱ ከፍተኛ ምርት ማምረቷን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ምርት ከ290 እስከ 340 ሚሊዮን ኩንታል (ከ29 እስከ 34 ሚሊዮን ቶን) በላይ መድረሱ ኢትዮጵያን በአፍሪካ አህጉር ቀዳሚ የስንዴ አምራች ሀገር አድርጓታል። የስንዴ ልማቱ አርሶ አደሩን ከቀድሞው ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ አላቆ፣ በኩታ ገጠም እርሻና በሜካናይዜሽን ታግዞ ወደ ሰፋፊ የንግድ ምርት እንዲገባ አስችሏል። የተሻሻሉ የስንዴ የሰብል ዝርያዎች መለቀቃቸው ለዚህ ውጤት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ የምርት አቅርቦት ሰንሰለቱን ማዘመን በቀጣይነት በትኩረት እየተሠራበት ይገኛል። በምርት አቅም እና በኩታ ገጠም እርሻ የተመዘገቡት እነዚህ ሰፊ ስኬቶች፣ ሀገሪቱ በኢኮኖሚ አቅም እያደረገችው ያለውን ሁለገብ ማንሰራራት በግልጽ የሚያሳዩ አብነቶች ናቸው። ይህ ትልቅ ለውጥ ኢትዮጵያ ከድህነትና ከዕርዳታ ጥገኝነት ወጥታ የምግብ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ ለሌሎች አፍሪካ ሀገራትም ተስፋ የሚሰጥ አህጉራዊ አርዓያ መሆን መቻሏን አስመስክሯል። ይህ የምርት እመርታ በግብርናው ብቻ ሳይሆን፣ አጠቃላይ የሀገሪቱን ማንሰራራት የሚያረጋግጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው። ለዘመናት በውጭ ዕርዳታና በለጋሾች ላይ ተወሰና የነበረችው ኢትዮጵያ፣ዛሬ በራሷ አቅም በመሥራት አህጉራዊ አርዓያ መሆን መቻሏ ትልቅ ስኬት ነው። የኢኮኖሚ ነፃነት እና የሉዓላዊነት ማዕቀፍን በማረጋገጥ ረገድም የስንዴ አብዮቱ የሀገርን አቅም የሚያሳይ ተምሳሌት ሆኗል። በመሆኑም በስንዴ ልማት የተገኘው ይህ ድል የግብርና ዘርፍ ስኬት ብቻ አይደለም፤ ኢትዮጵያውያን በቁርጠኝነትና በትጋት ከሠሩ ሀገርን ማሻገር እንደሚችሉ በተግባር ያረጋገጡበት ታላቅ የሀገር የማንሰራራት ማሳያ ነው።
የቡና ወጪ ንግድ እድገት - የኢትዮጵያ እመርታ አንዱ ማሳያ
Sep 5, 2026 386
ገና ወደ ውስጥ ሲገቡ ለምለም ቄጠማ በተጎዘጎዘበት ቤት እና ትኩስ በተቆላ ቡና ከደማቅ ፈገግታ ጋር አቀባበል ታደርጋለች። የቡናው ሽታ ደግሞ ልዩ መዐዛ አለው። አለምነሽ ሀብቱ ወደ ከተማ ከገባች በኋላ ድሮም የምትወደውን ቡና የሰርክ ስራዋ የእለት መተዳደሪያዋ አድርጋዋለች። ቡና ትወዳለች የአዘገጃጀት ድምቀቷንም ሌሎች ይወዱላታል። እሷ የምታዘጋጀውን የጀበና ቡና ለመጠጣት የመጣ ደንበኛዋ አትርፎ እንደወጣ እንዲሰማው የማድረግ ተሰጥኦ አላት። ቡና ትወዳለች ትጠጣለች ታጠጣለች ። እንደሷ ሁሉ ቡና ለኛ ለኢትዮጵያውያን አብሮን የሚውል፣ የሚያመሽ በብዙዎቻችን ቤት በቋሚነት የማይጠፋ ማህበራዊ መገናኛችን መመካከሪያችንም ጭምር ነው። በቡና ምርት በርካታ መሬትን ሸፍና ብዙ አርሶ አደሮችን እያሳተፈች የወጪ ንግዷን ለማሳደግ የምትጥረው ኢትዮጵያ ደግሞ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የምታገኝበት ዋንኛ የግብርና ኢኮኖሚው የጀርባ አጥንትም ነው። ባለፉት ዓመታት የቡና ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ድርሻም እያሳደገ መምጣቱን የተለያዩ መረጃዎች እያሳዩ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄ ማብራሪያ ሲሰጡ ለቡና ልማት የተሰጠው ትኩረት ኢትዮጵያን በአለም ሶስተኛዋ ቡና ላኪ ሀገር እንድትሆን ማስቻሉን ማንሳታቸው ይታወሳል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ከቡና ወጪ ንግድ የተገኘው ከ3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ወደ ውጭ ከላከቻቸው ምርቶች ከፍተኛው እንደነበረም አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከብራዚልና ከኮሎምቢያ በመቀጠል በዓለም 3ኛዋ ትልቋ የቡና ላኪ ሀገር መሆኗን እና በአፍሪካም ቀዳሚ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የሀገር ውስጥ የቡና ፍጆታ ከመቻል አልፈን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የመጣው ለውጥ የሀገራዊ የሪፎርሙ ስኬት መገለጫ ነው ማለታቸውም ይታወሳል። ይህ የአንድ ዓመት ምርት እንግዲህ ኢትዮጵያ ባለፉት 17 አመታት ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ካገኘችው 3 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ጠቅላላ ገቢ ጋር ሲነጻጸር አስደማሚ ስኬት መሆኑ አያጠራጥርም። አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለቡና ኤክስፖርት እድገት ስኬት አስተዋጽኦ ማበርከቱን በወቅቱ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቡናን ካልተከልን ፤ ካልተንከባከብን ፤ካልለቀምን፤ ካላጠብን፤ካላሸግንና ካላጓጓዝን ይህ ውጤት ሊመጣ አይችልም ብለውም ነበር። ኢትዮጵያ የአረቢካ ቡና መገኛ እንደመሆኗ የምርቱን እድገትና ዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ተፈላጊነቱን ለማሳደግ እየተከናወኑ ባሉ ተከታታይ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል። ባለፉት ተከታታይ ዓመታት የተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በሌሎች ኢኮኖሚያዊ፣ አካባቢያዊና የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳራዊ ግዙፍ አበርክቶው እንዳለ ሆኖ በቡና ምርት እድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ለዚህ ማሳያው ደግሞ መርሃ-ግብሩ ሲጀመር በ2011 ዓ.ም. ስድስት መቶ ሺህ ችግኝ የተተከለ ሲሆን ዓመታዊ ምርቱም 5 መቶ ሺህ ሜትሪክ ቶን ነበረ። በወቅቱ የተገኘው የውጭ ምንዛሪም 738 ሚሊዮን ዶላር ነበር። ይሄ ትኩረት በመቀጠሉም የቡና ችግኝ የመትከሉ ስራ አድጎ በ2017 ዓ.ም. ላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን በዛው ዓመት 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ተችሏል። ከላይ እንደተገለጸው የ2018 የቡና ወጪ ንግድ ገቢ 3 ነጥብ 1 መድረሱ ለዘርፉ የተሰጠውን ትኩረት እና የተመዘገበውን እመርታ የሚያሳይ ነው። ለዓመታት በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የቆየው የቡና ወጪ ንግድ ገቢ በአጭር ጊዜ መለወጥ እና ኢትዮጵያ ወደ ተለያዩ ሃገራት ከምትልካቸው የግብርና ምርቶች ከፍተኛውን ድርሻ ይዞ መቀጠሉ ለዘርፉ ለተሰጠው ትኩረት እና ለተገኘው ውጤት አንዱ መገለጫም ነው። የኢትዮጵያ ቡና በዓለም ገበያ ላይ ተፈላጊነቱ በየጊዜው እየጨመረም ይገኛል። ጀርመን፣ አሜሪካ፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ጃፓን፣ ቤልጂየም እና ደቡብ ኮሪያ ከቀዳሚዎቹ የኢትዮጵያ ቡና ገዢዎች መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን በቻይና እና በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የቡና ፍጆታና የመጠጣት ባህል በፍጥነት ማደጉ ለኢትዮጵያ አዳዲስ የገበያ እድሎችን ፈጥሯል። ይህ የኢትዮጵያ የእመርታ ጉዞ በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል ብልጽግናዋንም የምታረጋግጥ የዳበረ ኢኮኖሚ ያላትና የበለጠ ጠንካራ ሀገርነቷን የምታስቀጥልበት አዲስ ምዕራፍም ነው።
ለኢትዮጵያ የቤት ልማት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ስምምነት
Sep 4, 2026 374
የኢትዮጵያ የከተሞች ዕድገት ፈጣን እየሆነ በመምጣቱ እና የሕዝብ ቁጥር ዕድገት ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ በመሄዱ፣የዜጎችን የቤት ባለቤትነትን ጥያቄ በዘላቂነት መመለስ የመንግሥት አንዱ ዋና የትኩረት አቅጣጫ ሆኗል። ባለፉት ዓመታት የነበረው የቤት አቅርቦት በመንግሥት ትከሻ ላይ ብቻ የወደቀ በመሆኑ፣ ካለው ሰፊ የሕዝብ ፍላጎት ጋር አብሮ ለመሄድ ፈታኝ ሆኖ ቆይቷል። ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት መንግሥት አዲስ የቤት ልማት ፖሊሲ ቀርጾ በካቢኔ ማጽደቁ ይታወቃል። ፖሊሲው የዕድገቱን ፍጥነት እና የከተሞችን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ ነው። በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እየተከናወኑ ያሉ የኮንስትራክሽንና የከተማ ልማት ሥራዎች ለዚህ ሰፊ ራዕይ ግልጽ ማሳያዎች ናቸው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ በመላ ሀገሪቱ 1.2 ሚሊዮን ቤቶችን መገንባት መቻሉን አስታውሰዋል። ይህንኑ ስኬት መሠረት በማድረግ፣ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን አዳዲስ ተመጣጣኝ መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት መንግሥት አጠቃላይ ዝግጅት አድርጎ እየሠራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። አሁን ላይ አዲስ የግንባታ ቴክኖሎጂንና የረጅም ጊዜ የቤት ብድር ሥርዓትን በማስተዋወቅ የዜጎችን የቤት ባለቤትነት ጥያቄ በዘላቂነት ለመመለስ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። አዲሱ የቤት ልማት ፖሊሲ ተቀርጾ በካቢኔ መጽደቁንና በሁሉም ክልሎች የተቀናጀ ንቅናቄ መጀመሩን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ግንባታው በመንግሥት በጀት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን፣ የግሉ ዘርፍ እንዲሁም የመንግሥትና የግል አጋርነት መዋቅሮችን በስፋት መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የዜጎችን የመግዛት አቅም ያገናዘበና ፍላጎታቸውን የሚያስተናግድ አዲስ የፋይናንስ አሠራር መፈጠሩን ጠቅሰው፤ሰዎች ቤት በቀጥታ መግዛት ካልቻሉ በመንግሥት በሚመቻቸው አዲስ የሞርጌጅ ሥርዓት አማካኝነት ከገቢያቸው ላይ እየከፈሉ በረጅም ጊዜ ሂደት የቤት ባለቤት የሚሆኑበት ዕድል ይፈጠራል ብለዋል። ይህ ግብ የዜጎችን የቤት ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ የግሉን ዘርፍ በስፋት በማሳተፍ የሚሳካ መሆኑ በግልጽ ተቀምጧል። የሞርጌጅ ሥርዓት የቤት ፍላጎትን ለማሟላት የቀረበ ሌላኛው አማራጭ ሆኗል። የቤት መግዣ ብድር ሥርዓት (ሞርጌጅ) ማለት አንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ለመግዛት የሚያስፈልገውን ገንዘብ ከባንክ በብድር አግኝቶ፣ ያንን የተበደረውን ገንዘብ ከነወለዱ በረጅም ዓመታት መልሶ የሚከፍልበት የፋይናንስ አሠራር ነው። ይህ አሠራር አቅማቸው ውስን ለሆኑ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በወር በወር እየከፈሉ የቤት ባለቤት የመሆን ልዩ ዕድል ይፈጥራል። የከፍተኛ የቤት ኪራይ ወጪን በማስቀረት ዜጎች በየወሩ የሚከፍሉት ገንዘብ በራሳቸው ንብረት ላይ የሚደረግ ጠቃሚ ኢንቨስትመንት እንዲሆን ያደርጋል። ይህንን ታላቅ ራዕይ ከግብ ለማድረስ በዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መካከል በሀገሪቱ የመጀመሪያው የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ተፈጽሟል። በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅዖ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፉ ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው ገልጸዋል። ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት የተቀመጠውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን እንደምትቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። የዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ማክታር ዲዮፕ በሰጡት አስተያየት፣ ይህ አጋርነት በኢትዮጵያ የከተሞች ልማት ላይ የግል ባለሀብቶች በስፋት እንዲሳተፉ ትልቅ ምቹ ምህዳር እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ጠንካራ የቤት ፋይናንስ ገበያ የዜጎችን ሕይወት ለማሻሻል እና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለመደገፍ ቁልፍ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳዩ እንዲጀመር እንዲሁም ሂደቱ ላይ ክትትል በማድረግ እያከናወኑት ላለው ሥራና አመራር ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በዚህ የፋይናንስ ማዕቀፍ አማካኝነት ዜጎች ሙሉ የቤት መግዣ ገንዘብ እስኪኖራቸው ሳይጠብቁ በባንክ ብድር የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ይደረጋል።ግንባታው በመንግሥት በጀት ብቻ ሳይሆን በመንግሥት፣ በግል ዘርፍ፣ እንዲሁም በመንግሥትና በግል አጋርነት (PPP) ይከናወናል። የሞርጌጅ ፋይናንስ ሥርዓቱ የዜጎችን ማህበራዊ ዋስትና በማረጋገጥ የባለቤትነት ስሜት ከመፍጠር አኳያ ያለው ፋይዳ ቁልፍ የሚባል ነው። መንግሥት ብቻውን ሊያከናውነው የሚችለውን ግዙፍ የልማት ጫና፣የግሉን ዘርፍ እና ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማስተባበር በጋራ መወጣት እንደሚቻል የዛሬው ስምምነት ግልጽ ማሳያ ነው። የ100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ፈንድ እና የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ዕቅድ እውን መሆን፣ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ጉዞ የሚያፋጥንና ሁሉንም ዜጎች አካታች የልማት ባለቤት የሚያደርግ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
የኮሪደር ልማት እና የነገዋ ኢትዮጵያ
Sep 4, 2026 283
በኢትዮጵያ አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች መጻኢውን ጊዜ ብሩህ ለማድረግ መሰረት የሚጥሉ ናቸው። ከእነዚህ ስራዎች በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው የሀገሪቱን ከተሞች ገጽታና የነዋሪዎቿን የኑሮ ዘይቤ በከፍተኛ ደረጃ እየቀየረ ያለው የኮሪደር ልማት መርሃ ግብር ነው። ይህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የኮሪደር ልማት ከተሞችን ለኑሮ ምቹ፣ ንጹህና ስልጡን በማድረግ ትልቅ ምዕራፍ ከፍቷል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ያስመዘገበው ስኬትና የፈጠረው አርአያነት አሁን ላይ አዲስ አበባን አልፎ በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች ተግባራዊ ተደርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ የኮሪደር ልማት ከከተማ ውበትና ገጽታ ባለፈ የሀገሪቱን የዕድገት አቅጣጫ በከፍተኛ ደረጃ እየቀየረ ያለ እና የነገዋን ሀገር ዛሬ ላይ የመቅረጽ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው። በኮሪደር ልማቱ ለእግረኛ እና ለአካል ጉዳተኞች ፈታኝ የነበሩ መንገዶች ዛሬ ሰፊና ጥራት ባላቸው የኮንክሪት ንጣፎችና የብስክሌት መስመሮች ተተክተዋል። በከተሞች የሚገኙ የመዝናኛ ፓርኮች፣ የማረፊያ ስፍራዎች እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ቦታዎች የዜጎችን ማኅበራዊና ሰብአዊ ክብር ከፍ ያደረጉ ሲሆን፤ እነዚህ ጥራት ያላቸው መሠረተ-ልማቶች የነገውን ጤናማ እና ማህበራዊ ፍትሕ የሰፈነበት ማህበረሰብ ለመፍጠር የተጣሉ ጠንካራ መሠረቶች ናቸው። የኮሪደር ልማት የከተሞችን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ወደ ዘመናዊነት በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በዘመናዊ የጎዳና ላይ መብራቶችና የደህንነት ካሜራዎች የታገዙ ከተሞች በቀን ብቻ ሳይሆን በሌሊትም የንግድና የኢኮኖሚ ማዕከል እንዲሆኑ በር በመክፈታቸው፣ የ24 ሰዓት የስራ ባህልን በመፍጠር ለአያሌ ወጣቶችና አነስተኛ ነጋዴዎች አዲስ የሥራ ዕድል ፈጥረዋል። በሌላ በኩል፣ ይህ ስትራቴጂካዊ ልማት ኢትዮጵያን ወደ ቋሚ የኮንፈረንስ፣ የንግድ እና የባህል ቱሪዝም መዳረሻነት እየቀየራትም ይገኛል። በተለይም የከተሞችን ማህበራዊ መስተጋብርና የሕዝቡን አንድነት በማጠናከር ረገድ የኮሪደር ልማቱ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ ነው። በልማቱ የተፈጠረው የጋራ ትስስር የነገዋን ጠንካራ፣ ሰላማዊና በአብሮነት የታነጸች ሀገር ለመገንባት እንደ ትልቅ ማህበራዊ መሰረት ያገለግላል። የነገዋ ኢትዮጵያ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም ያደገችና አሰራሯ የዘመነ መሆኑን የሚያረጋግጥ ተግባራዊ እርምጃ ከኮሪደር ልማቱ ጋር ተሳስሮ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል። ስራው ከቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በቅንጅት በማከናወን ዘመናዊ የትራፊክ ቁጥጥር ሥርዓቶች እና የስማርት ከተማ መተግበሪያዎች መሰረተ ልማት አብሮ እየተዘረጋ ይገኛል። በተጨማሪም ከኮሪደር ልማት ጋር እየተከናወነ ያለው መጠነ ሰፊ የአረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዞች ዳርቻ ልማቶች ከተሞች ከአየር ንብረት ለውጥ ስጋትና ሙቀት በመከላከል ለትውልዱ ንጹህና ጽዱ መኖሪያን አካባቢን ለማስረከብና ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት እያስቻለ ነው። በአጠቃላይ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከአንድ ከተማ ገጽታ ማሻሻል ባሻገር፣ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ በርካታ ክልል ከተሞች ላይ በመስፋፋት ሀገራዊ ለውጥ ፈጥሯል ማለት ያስችላል። የዚህ ዘርፈ ብዙ የልማት ፍሬ ዛሬ ላይ የኑሮ ዘይቤን እያሻሻለ እንደሚገኘው ሁሉ፣ ለወደፊቱ ትውልድም የኩራት ምንጭ የሆነ ዘላቂ ሀብት ሆኖ ይሸጋገራል። ዛሬ በጥራትና ውብ ሆነው እየተሰሩ ያሉ መንገዶች፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች እና የዲጂታል መሰረተ ልማቶች የነገዋ ኢትዮጵያ የበለጸገች፣ ስልጡንና ለኑሮ ምቹ የማድረግ ራዕይን እውን የሚያደርጉ ናቸው።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 12921
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 22269
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 15300
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 21044
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ የማዕድን ምርት እመርታ
Aug 21, 2026 1247
በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአገር በቀል የኢኮኖሚና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ታግዞ፣ ባለፉት ዓመታት የታዩበትን የአሰራርና መዋቅራዊ ችግሮች በመቅረፍ ከፍተኛ የመነቃቃት ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ዘርፉ በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ ማዕድን በብዝኃ ዘርፍ የልማት ምልከታችን ውስጥ እና በሀገሪቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል። ባለፉት ሶስት አሥርት ዓመታት ውስጥ የማዕድን ዘርፉ ለአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያበረከተው አስተዋጽኦ ከ0 ነጥብ 8 በመቶ በታች የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ግን መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው የላቀ ትኩረት ከፍተኛ መዋቅራዊ ሽግግር እያመጣ ይገኛል። በ2018 በጀት ዓመት ከዘርፉ 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ተችሏል። ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ92 በመቶ የገቢ ዕድገትና የ27 በመቶ የምርት መጠን ብልጫ ያሳየ ሲሆን፣ ምርቶቹም በዋናነት ወደ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ አሜሪካ፣ ጀርመን እና ቻይና ተልከዋል። በወጪ ንግድ እድገት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው የወርቅ ምርት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ለውጭ ገበያ የቀረበ ሲሆን እስከ ዓመቱ ማብቂያ 32 ቶን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። በባህላዊ መንገድ የሚመረተውን የወርቅ ምርት ለማዘመንም መንግሥት የማጣሪያና ማቀለጫ ፋብሪካዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል። የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ከውጭ የሚገቡ ስትራቴጂክ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህም ለድንጋይ ከሰል ግዢ ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት የተቻለ ሲሆን፣ የሲሚንቶ ምርትም ባለፉት ስምንት ዓመታት ከነበረበት 8 ሚሊየን ቶን አሁን ላይ በዓመት ወደ 14 ሚሊየን ቶን አድጓል። ሀገሪቱ በየዓመቱ ለማዳበሪያ ግዢ የምታወጣውን 2 ቢሊየን ዶላር ለማስቀረትም የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ተጀምሯል። በተጨማሪም በየዓመቱ ለብረት ምርት ግዢ የሚወጣውን 1 ቢሊየን ዶላር በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት የሚያስችል ግዙፍ ፋብሪካ የመገንባት ስምምነት ተፈጽሞ ወደ ስራ ተገብቷል። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በዘርፉ የተሰማሩ ፕሮጀክቶች ዋጋ 10 ቢሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከለውጡ በፊት ከነበረውና ከ100 ሚሊየን ዶላር የማይበልጡ አነስተኛ ኢንቨስትመንቶች በከፍተኛ ደረጃ የለወጠ ስኬት ነው። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በአፋር ክልል የሚገኘውን ግዙፍ የፖታሽ ክምችት ለማልማት ፈቃድ አግኝቶ ወደ ሥራ ገብቷል። በተጨማሪም ታንታለምን እሴት ጨምሮ ለመላክ ከአሜሪካ ኩባንያ ጋር ድርድር እየተደረገ ሲሆን፣ ለባትሪና ቴክኖሎጂ ወሳኝ የሆኑትን ሊቲየም፣ ኮባልትና ኒኬልን ለማምረት ዝግጅት ተጠናቋል። የኢንቨስትመንት ምህዳሩን ሳቢ ለማድረግ የማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ አሰራር ቅድሚያ የመጣን ቅድሚያ ማስተናገድ በሚል መርህ እንዲመራ ተደርጓል። የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና መላኪያ ፈቃዶች፣ እንዲሁም የካዳስተር ሲስተም ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ አሰራር ተሸጋግረዋል። በ2019 በጀት ዓመት ከዘርፉ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፣ የመንግሥት ስትራቴጂካዊ እቅድ እ.አ.አ. በ2030 የማዕድን ወጪ ንግድ ገቢን ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ በማድረስ ኢትዮጵያን ከአፍሪካ አምስት ቀዳሚ የማዕድን አምራች ሀገራት ተርታ ማሰለፍ ነው። በዘርፉ እየተካሄደ ያለው መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ በውጭ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኝነት በመቀነስ ወደ ኢንዱስትሪ መሪነት የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥነዋል። የወርቅ፣ የተፈጥሮ ጋዝ፣ የፖታሽ እና የቴክኖሎጂ ማዕድናት በሀገር ውስጥ እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ላይ የሚኖራትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ያረጋግጣል።
የአረቡ ዓለም ከግብፅ ምን አተረፈ?
Aug 19, 2026 976
የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ አካሄድ በታሪካዊ እውነታዎች እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ላይ እየተመሠረተ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ ጊዜ ያለፈባቸው የጂኦ ፖለቲካዊ የመጠላለፍ አካሄዶች ዋጋ ቢስነትና ጥቅም አልባነት በግልጽ እየታየ ይገኛል። ለብዙ አስርት ዓመታት ግብፅ የዓረብ ሊግን ለራሷ ጠባብ ፍላጎቶች እና ጂኦፖለቲካዊ አጀንዳዎች ማስፈጸሚያነት በሰፊው ስትጠቀምበት ቆይታለች። ሆኖም ይህ ጥቅምና ጉዳትን ብቻ መሰረት ያደረገ ግንኙነት አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ያስነሳል፦ ለመሆኑ የዓረቡ ዓለም ከግብፅ በምላሹ ያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? ለዚህ ጥያቄ አጭሩ መልስ ምንም የሚል ነው ሲል “What Has the Arab World Gained from Egypt? Why Ethiopia Belongs in the Arab League?” ፀሐፊው እና በፖለቲካና ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ በቋሚነት የሚተነትነው አስተያየት የሚሰጠው ጅብሪል ላሞ በኢዜአ እንግሊዘኛ ገጽ ባሳፈረው ሐተታ ላይ ፣ የግብጽ ፖሊሲዎች እንዲሁም ለሁለት አስርት ዓመታት የዘለቀው አምባገነናዊ አስተዳደር የጋራ ጥንካሬን ከመፍጠር ይልቅ የቀጣናውን አለመረጋጋት ማባባሳቸውን ገልጿል። እነዚህ ፖሊሲዎች፣ በምሥራቅ አፍሪካ እና በቀይ ባሕር አካባቢም ውጥረትን እያባባሱ እንደሚገኙ አመልክቷል። እነዚህ አካባቢዎች ለዓረቡ ዓለም የራቁ አይደሉም፤ ይልቁንም ለዓረቡ ዓለም ደኅንነት፣ የባሕር ንግድ፣ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የምግብ ዋስትና እጅግ ወሳኝ እና ስትራቴጂካዊ ማዕከላት ናቸው። የግብፅ ከፋፋይ ቀጣናዊ አካሄድ ከታዩባቸው ጉልህ ማሳያዎች አንዱ በኤርትራ ጉዳይ እና በሰፊው የኢትዮጵያ ግዛት አንድነት ላይ የነበራት ታሪካዊ ጣልቃ ገብነት ነው። ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ቀጣናዊ ተፅዕኖዋን ለመግታት በግብጽ ታስበው የተደራጁ ተገንጣይ ኃይሎችን እና ፖለቲካዊ ፕሮጀክቶችን በግልጽ ትደግፍ እንደነበረ ፀሐፊው አውስቷል። ከኢትዮጵያ የኤርትራ መገንጠል በምሥራቅ አፍሪካ ቀውስ የተሞላ ታሪክ ውስጥ አቢይ ክስተት ሲሆን፣ የውጭ ጂኦፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነቶች የሀገራትን እጣ ፈንታ እንዴት እንደሚያናጉ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የዲፕሎማሲ ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ የቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ እና የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ፣ ኢትዮጵያን ለማዳከም ታስቦ የተዘረጋውን የኤርትራን የመገንጠል ፕሮጀክት በመደገፍና በማፋጠን ረገድ ትልቅ ሚና ነበራቸው። በተጨማሪም ግብጽ በደቡባዊ የቀይ ባህር ቀጣና የምታካሂደው ቀውስ የመፍጠር እንቅስቃሴ፣ ለዓለም አቀፍ የባህር ንግድና ለቀጣናው ደህንነት ቀጥተኛ ስጋት ደቅኗል። በባብ-ኤል-ማንደብ የባሕር ወሽመጥ አካባቢ ውጥረቶችን በመቀስቀስ እና ተላላኪ ታጣቂ ቡድኖችን በማንቀሳቀስ፣ ወሳኝ የሆኑ የባህር መተላለፊያዎችን የጂኦፖለቲካዊ ግጭት መድረክ አድርጋዋለች። ይህም ለጠቅላላው የዓረብ ዓለም የኢነርጂና የምግብ አቅርቦት መሰረት የሆነውን የደህንነት መዋቅር አደጋ ላይ ጥሎታል፤ ሲሉ ጅብሪል ላሞ ያብራራሉ። ጅብሪል ላሞ በጽሑፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ የግብፅ ግልጽ የራስ ወዳድነት እንቅስቃሴዎች ቀጣናዊ ውጥረትን የሚፈጥሩ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ መቀላቀል ግን ለዓረቡ ዓለም እጅግ ከፍተኛ ጥቅም የሚያስገኝ ለውጥ አምጪ ዕድል ይዞ ይመጣል። በመደመር ፍልስፍና አሳታፊ ማዕቀፍ ሥር፣ ኢትዮጵያ ከማግለል ፖሊሲ ይልቅ የዓረቡን ዓለም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማስተሳሰር የሚያስችል የላቀ የዲፕሎማሲ አቅም አላት። በዚህም የአፍሪካ ዋነኛ የዲፕሎማሲ ማዕከል እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ የባለብዙ ወገን ትብብሮችን በመቅረጽ ረገድ ያላትን የካበተ ልምድ ታካፍላለች። የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ የመቀላቀል ጥረት ጊዜያዊ የፖለቲካ ስሌት ሳይሆን፣ የተፈጥሮ የታሪክ ጥሪ ነው። ከ135 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ፣ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እና ጥልቅ የሥልጣኔ መሠረት ያላት ይህች የቀይ ባሕር ሀገር፣ አባልነቷ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ መካከል ስትራቴጂካዊ ድልድይ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር ያላት ቁርኝት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በጋራ ታሪክ፣ ባህል እና የደም ትስስር ላይ የተገነባ ነው። እንደ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሉ የትምህርት ተቋማት፣ የኢትዮጵያ ጥናቶች በታሪክ ደረጃ ከመካከለኛው እና ከቅርብ ምሥራቅ ታሪክ (Near Eastern Studies) ተመድቦ መጠናቱ፤ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ከቀጣናው ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ ውህደት የሚያረጋግጥ ሕያው ማሳያ ነው። የባብ-ኤል-ማንደብ የባህር ወሽመጥ በጭራሽ መሰናክል አልነበረም፤ ይልቁንም ንግድን፣ ባህልን እና ማህበረሰቦችን በቀይ ባሕር በኩል ያገናኘ ዋንኛ መተላለፊያ ሆኖ አገልግሏል። ከንጉሥ አብረሃ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ በኢትዮጵያውያን እና በመካከለኛው ምሥራቅ ሕዝቦች መካከል የጋራ የደም ትስስር እንደነበር የሚያረጋግጡ ዘመናዊ የስነ ህይወት( ጄኔቲክስ) ጥናቶች፣ የዚህን ታሪካዊ ቁርኝት እውነተኛነት በግልጽ ያሳያሉ። በቋንቋና በባህል ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት መሠረት ታሪካዊ ትስስር ያለው ነው። የሀገሪቱ የቋንቋና የሥነ-ጽሑፍ ውርስ ከዓረብኛ፣ አራማይክና ዕብራይስጥ ጋር በጽኑ የተሳሰረ ሲሆን፣ ይህም በምሥራቅ አፍሪካና በአረቢያ ልሳነ-ምድር መካከል ያለውን ጥልቅ የጋራ የሥልጣኔ ቁርኝት ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ አላት። የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ተስደው በንጉስ ነጃሺ ከለላ ማግኘታቸው የእስልምናን ህልውና የታደገ ታሪካዊ ክስተት ሲሆን፣ ይህም ሀገሪቱን ከዓረቡ ዓለም ጋር በጽኑ አስተሳስሯታል። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ የዓረብ ሊግን በኢትዮጵያ ላይ እንደ ተቋማዊ ተፅዕኖ ማሳደሪያ መሣሪያ ግብጽ ስትጠቀምበት ቆይታለች። ግብፅ የውጭ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ዕድገት፣ የህዳሴውን ግድብም ሆነ የባሕር በር ጥያቄን እንደ ሥጋት በሚያይ ጊዜ ያለፈበት ስሌት ላይ የተመሠረተ ነው። ግብፅ የራሷን የውሃ አቋም በሊጉ ላይ በመጫን፣ ተቋሙ ከኢትዮጵያ ጋር አላስፈላጊ ውጥረት ውስጥ እንዲገባ አድርጋለች። ጅብሪል ላሞ እንዳመለከተው፣ ከግብጽ የአግላይነት ፖሊሲ ይልቅ የዘመኑ ነባራዊ ሁኔታዎች ሙሉ ትብብርን የሚጠይቁ ናቸው። በመደመር መርህ፣ ኢትዮጵያ ለዓረቡ ዓለም ለዘመናት ከቆዩ የጥላቻ መንገዶች በላቀ ሁኔታ የተሻሉ ጥቅሞችን ማቅረብ ትችላለች። እያደገ የመጣው የኢንዱስትሪ እና የአረንጓዴ ኃይል አቅሟ፣ ኢትዮጵያን ለቀይ ባህር ቀጣና የመረጋጋት ምሰሶ አድርጓታል። የመካከለኛው ምሥራቅ ቀጣና የውሃ እጥረት እና የምግብ ዋስትና ሥጋት በተጋረጠበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ የውሃ ሀበት እና ለም መሬት ለቀጣናው ወሳኝ የግብርና-ኢንዱስትሪ አጋር ያደርጋታል። የዓረብ ሊግ አባል ሀገራት የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ብሔረተኝነት በመሻገር፣ የቀይ ባህርን ቀጣና የሥልጣኔ እውነታ መቀበል ይኖርባቸዋል። አረብ ሊግ እንደ ጅቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ኮሞሮስ እና ሞሪታኒያ አባል ሀገራት መያዙ፣ ስብስቡ የተለያዩ ቀጣናዊ እውነታዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑን ያሳያሉ። የዓረብ ሊግ ሙሉ አባልነት የኢትዮጵያን አፍሪካዊ ማንነት ሳይቀንሰው፣ አህጉሩን ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር የሚያገናኝ ዋነኛ ድልድይ የሚያደርጋት በመሆኑ፤ ሊጉ የኢትዮጵያን አጋርነት በመቀበል ለአዲስ አበባ ተገቢውንና ሕጋዊ ቦታዋን የሚሰጥበት ጊዜ አሁን እንደሆነ በመግለጽ ጅብሪል ላሞ ፅሁፉን ቋጭቷል።