ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በአማራ ክልል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎትን ማቀላጠፍ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Dec 31, 2025 5
ደብረ ማርቆስ፤ ታህሳስ 22/2018 (ኢዜአ)፡ -በአማራ ክልል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎትን ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ የዲጅታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማጎልበት ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በደብረማርቆስ ከተማ አካሄዷል። የክልሉ ሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ኃላፊ ማዓዛ በዛብህ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የክልሉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን በጠራ መረጃ ለማስደገፍ እየተሰራ ነው። ለዚህም በ8 "ሪጅኦ ፖሊታንት" ከተሞች በ204 ጣቢያዎች የተጀመረውን ሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ዲጅታላይዝድ በማድረግ ባለፉት 5 ወራት ብቻ ከ450 ሺህ በላይ የሞት፣ ጋብቻ፣ ፍቺና ልደት ኩነትን መመዝገብ መቻሉን አስረድተዋል። የአሰራሩ ዲጂታላይዝ መደረጉም ከዚህ ቀደም በዓመት ለቅጻቅጽ ግዥ ይወጣ የነበረን ከ3 ሚሊየን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ብለዋል። በመጀመሪያው ዙር የተገኘውን ተሞክሮ በማስፋት የ2ኛውን ዙር የዲጅታል ምዝገባ ስርዓት አጠናክሮ ለማስቀጠል የዛሬው መድረክ መከናወኑንም ገልጸዋል። የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ በበኩላቸው፤ ዲጅታል ኢትዮጵያ ቦዞኑ በአገልግሎት አሰጣጥ የነበረውን የተንዛዛ አሰራር መቀነስ አስችሏል ብለዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም የምዝገባ ሂደቱን በዲጅታል በማከናወን ግልጽና ታማኒነት ያለው መረጃን ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ለማድረግ አቅም የሚፈጥር ነው ሲሉ ተናግረዋል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ፤ የከተማ አስተዳደሩ በገቢዎች፣ በሲቪልና በቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት፣ በካዳስተርና ሌሎች የስራ መስኮች የዲጅታል አገልግሎት እየተገበረ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የሀረር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ የተቀናጀ ርብርብ እየተደረገ ነው
Dec 31, 2025 20
ሀረር፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በሀረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ የተቀናጀ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ በሀረር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከጉብኝቱ በኋላ እንደተናገሩትም የሀረር ከተማን ድምቀትና ውበት ይበልጥ የሚያጎናጽፉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል። ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ እንዲሁም ለመጪው ትውልድ መሰረት የሚጥሉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው የኮሪደር ልማት ስራው አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ዙሪያ የቅርሱን ይዘት በጠበቀ መልኩ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ቅርስን ጠብቆ ከማቆየት ባለፈ ትውልዱ በታሪክ እንዲወሳ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸው የተጀመሩ የልማት ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የተከናወኑና በሂደት ላይ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች የተሽከርካሪና የእግረኛ መንገዶች፣ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ ፋውንቴኖች፣ የፍሳሽ ማስወገጃዎች፣ የአረንጓዴ ስፍራና የመንገድ ዳር መብራትን ያካተቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ የተቀናጀ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በሚሰሩ ስራዎች ህዝቡ እያደረገ የሚገኘው ትብብርና ድጋፍ ስራውን ከማገዝ ባለፈ ለበለጠ ውጤት የሚያነሳሳ መሆኑንም አስረድተዋል። በየአካባቢው እየተከናወኑ ለሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች መሰረተ ልማት እንዲሟላ ከማስቻል ባሻገር ህገ ወጥነትን ለመከላከል ጭምር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
የክልሉን እምቅ የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ለማስደገፍ ትኩረት ተድርጓል
Dec 31, 2025 28
ዲላ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ያለውን እምቅ የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ለማስደገፍ ትኩረት መደረጉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ልማት አቅም ልየታ ላይ ያተኮረ መርሃ ግብር በዲላ ከተማ የተካሄደ ሲሆን ከውይይት መድረኩ በኋላ በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ ቱማታ ጭራቻ ቀበሌ 60 ሄክታር የቡና ኩታ ገጠም እርሻ የመስክ ምልከታ ተደርጓል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በማጠቃለያው እንዳሉት የክልሉን እምቅ የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ማስደገፍ ወሳኝ ነው። በተለይ በክልሉ ያለውን ሰፊ መሬትና የውኃ ሀብት ከቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ወደ ተግባር ለመለወጥ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል። ክልሉ በግብርና ልማት ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ አምራች እንዲሆን ጥናትና ምርምርን መሰረት ያደረገ ስራ እንደሚሰራ አመልክተው የዛሬው መድረክም ይህንኑ ለማጠናከር የተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ የቀረቡ ምክረ ሀሳቦችን በመተግበር ከፍተኛ ምርት ለማምረት የዘርፉ ባለድርሻ አካላትና አመራሩ በቅንጅት መስራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለግብርና ልማት ምቹ የሆነ ተፈጥሮ የታደለ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ናቸው። የግብርና አቅሞችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ የአርሶ እና አርብቶ አደሩን ህይወት በመለወጥ ሀገርን ማሳደግ እንደሚቻልም ጠቅሰዋል። በተለይም የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም በኩል በክልሉ የሚስተዋለውን ውስንነት በመቅረፍ የግብርና ሽግግርን ማፋጠን እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በእውቀት ላይ በመመስረት የሚከናወን የግብርና ልማት ስራ የኢትዮጵያን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሳካት ዋሳኝ ሚና እንደሚጫወትም አክለዋል።
በሀገራዊ ወግና ባህል የተቃኘ፣ ከዓለም እኩል መራመድ የሚያስችል ትምህርትና ሥልጣኔን ለማጠናከር በትኩረት ይሰራል
Dec 31, 2025 26
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ወግና ባህል የተቃኘ፣ ከዓለም እኩል መራመድ የሚያስችል ትምህርት፣ ቴክኖሎጂና ሥልጣኔ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ይገኛል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በ75 ዓመታት ጉዞው ከ300 ሺህ በላይ ምሩቃንን በማፍራት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ዘርፎች ላይ የራሱን አሻራ አሳርፏል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዩኒቨርሲቲው ከሀገር መሪዎች እስከ ዓለም አቀፍ ተመራማሪዎችን ያፈራ የሀገር ባለውለታ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ የተሳለጠ የውጭና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መንገድ አሳይቷል፤ ለግብርናና አካባቢ ጥበቃ ስራዎች ሀሳብ አዋጥቷል፣ ለትምህርትና ስልጠና ስርዓት መሻሻል መሰረት ጥሏል ብለዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው 75ኛ ዓመት በዓል ሲከበር ስራዎችን ለመዘከርና ታረክ ለመንገር ብቻ አይደለም ያሉት ሳሙኤል (ዶ/ር)፤ ለሀገራዊ ብልጽግና አጋዥ ሀሳቦችን ለማለም ጭምር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ፤ የ75ኛ ዓመት ምስረታ በዓልና የራስ ገዝነት አስተዳደር የተገናኙበትን የታሪክ ግጥምጥሞሽም የቀጣይ ሥራዎችን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት መልካም ዕድል የፈጠረ ብለውታል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በራስ ገዝነት ያገኘውን ወርቃማ ዕድል በመጠቀም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ኃላፊነቱን ይወጣል ብለዋል፡፡ በቀጣይ ዩኒቨርሲቲው ያገኘውን የራስ ገዝነት ዕድልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመጥርና ለኢትዮጵያና ህዝቦች ዕድገት ገንቢ ሚና የሚወጣ ተቋም እንዲሆን ያስችለዋል ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ በሀገራዊ ወግና ባህል የተቃኘ፣ ከዓለም እኩል መራመድ የሚያስችል ትምህርት፣ ቴክኖሎጂና ሥልጣኔ ሊኖራት ይገባል ያሉት ሳሙኤል (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ለዚህ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የቀጣዩ ዘመን የመወዳደሪያ መድረክ መሆኑን ገልጸው፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ፕሮግራሙን በሶስተኛ ዲግሪ ደረጃ ማስተማር ጀምሯል ብለዋል፡፡ ይሄውም የመንግስት የፖሊሲ አቅጣጫዎች ማሳካትና ኢትዮጵያ በነባራዊው ዓለም ተወዳዳሪ የምትሆንበትን አውድ እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለመለወጥ በምታደርገው ጥረት በጥናትና ምርምር የታገዘ ድጋፍ በማድረግ ኃላፊነቱን መወጣቱን ይቀጥላል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው
Dec 31, 2025 26
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ገለጹ። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለአምስት ተከታታይ ቀናት የተካሄደው ሁለተኛው የብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ(ግሪን ሞቢሊቲ) አውደ ርዕይና ፎረም 2025 ተጠናቋል። በአውደ ርዕይና ፎረሙ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን፤ የዘንድሮው ዓውደ ርዕይ ዓላማውን ያሳካና ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተካሄዱ የውይይት መድረኮችም በርካታ አካላትን ያገናኙና ውጤታማ መረጃዎች የተለዋወጡባቸው መሆናቸውን ጠቁመዋል። በአውደ ርዕዩ ኢትዮጵያውያን በዘርፉ ላይ የላቁ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ሥራዎችን በማቅረብ ሻጮችና ሸማቾች የተገናኙበት ትልቅ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ ብሩህ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ሀገሪቱ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የጀመረቻቸውን ውጤታማ ሥራዎች አጠናክራ እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል። በአሁኑ ወቅት የአረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዓውደ ርዕዩ አዳዲስ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ መቅረባቸውንና ዘርፉ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም ያለውን ፋይዳ በተመለከተም የጋራ ግንዛቤ የተፈጠረበት እንደሆነ ገልጸዋል። ለአውደ ርዕዩ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ ተሳታፊዎች ምስጋና አቅርበው፤ በመጪው ዘመን በፈጠራው ዘርፍ የተሻሉ ሥራዎች እንደሚጠበቁም አመልክተዋል። ዓውደ ርዕዩ በቀጣይም ይበልጥ እንዲሳካ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ተጋላጭነት ለመውጣት የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭን ጨምሮ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማስፋፋት በኩል ውጤታማ የአረንጓዴ ልማት እርምጃዎችን እየወሰደች እንደምትገኝም በዚሁ ወቅት ተመልክቷል።
ፖለቲካ
በመሪዎች መካከል የተደረጉ ስምምነቶችን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው
Dec 31, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያና ህንድ መሪዎች መካከል የተደረጉ ስምምነቶችን ተግባራዊ ለማድረግ እና የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂክ አጋርነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ ገለፁ። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ማደጉ ከኢኮኖሚና ንግድ ባለፈ ያላቸውን የትብብር አድማስ የሚያሰፋ መሆኑንም ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለፁት፤ኢትዮጵያና ህንድ ለረጅም ዘመናት የዘለቀ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው። ኢትዮጵያ በህንድ የባህል ማዕከል ያላት ብቸኛ አፍሪካዊት ሀገር መሆኗን አንስተው፤ የኢትዮጵያን ባህል በህንድ የበለጠ ለማስተዋወቅ እንደሚሰራም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት ከ40 በላይ በረራ ወደ ህንድ እንደሚያደርግ የገለጹት አምባሳደሩ ተቋሙን የኢትዮጵያ የባህል አምባሳደር ሲሉ አሞካሽተውታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ናሪንድራ ሞዲ ጉብኝትን ተከትሎ የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ማደጉንም አስታውሰዋል። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ማደጉ ከኢኮኖሚና ንግድ ባለፈ የትብብር አድማስን የሚያሰፋ መሆኑን ጠቁመዋል። ጉብኝቱን ተከትሎ ሀገራቱ በጉምሩክ፣ በሰላም ማስከበር፣ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዳታ ማዕከል መገንባትን ጨምሮ የተለያዩ ስምምነቶች መፈራረማቸውንም አስታውሰዋል። የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ማደግ የደቡብ ለደቡብ ትብብርን የሚያጠናክርና ሀገራቱ ያላቸውን ዓለም አቀፍ አጋርነት የሚያጎለብት መሆኑን አስረድተዋል። በህንድ የትምህርት እድል የሚያገኙ ኢትዮጵያውያንን ቁጥር በእጥፍ ለማሳደግ ስምምነት ላይ መደረሱንም አንስተዋል። ሀገራቱ በጋራ ለመስራት የተስማሙባቸውን ተግባራት ለማስፈፀምና ስትራቴጂክ አጋርነቱን ለማጠናከር የሚያስችል ፍኖተ ካርታ እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግረዋል።
እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል-ኮሚሽኑ
Dec 30, 2025 218
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 21/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመ ጀምሮ ባከናወናቸው ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ሀገራዊ ምክክሩን ለመምራት ገለልተኛ ሆኖ መዋቀሩን ያስገነዘቡት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቃል አቀባይ ጥበቡ ታደሰ፤ እስካሁን ስኬታማ ተግባራት ማከናወኑን ለኢዜአ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ባለድርሻ አካላት ተለይተው በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ በማድረግ ረገድ በርካታ ውጤቶች የተገኙባቸው ሥራዎች ተሠርተዋል ብለዋል። አጀንዳ የተሰበሰበበት መንገድ በርካቶች የተስተናገዱባቸው መድረኮች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህም የዴሞክራሲ ልምምድን በማሳደግ የምክክር ሂደት እንዲዳብር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። የምክክር ሂደቱ የኢትዮጵያውያን እንዲሆንና ባለድርሻ አካላት የሂደቱ ባለቤት እንዲሆኑ የተሠሩ ሥራዎችም ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን ነው ያስገነዘቡት። በግልጽና ገለልተኛ አሠራር አካታችና አሳታፊ በሆነ መንገድ ተሳታፊዎችን መለየት መቻሉ ከተገኙ ውጤቶች መካከል መሆኑንም ጠቁመዋል። በውክልና የመሳተፍ ልምምዶችን፣ዴሞክራሲያዊ ባሕርይን የማምጣቱ ጉዳይም ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው መሆኑን አመላክተው፤ 93 በመቶ የኢትዮጵያ ወረዳዎችን በምክክር ሂደቱ ማሳተፍ መቻሉን አመላክተዋል። በሕዝቡ፣በባለድርሻ አካላት፣ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡም ጭምር ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ተቀባይነት እንዲኖረው የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት መሆኑንም ነው ያረጋገጡት። በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት እንደተጠበቁ ሆነው በሂደት ከኃይል አማራጭ ይልቅ ምክክር የተሻለ ውጤታማ ያደርጋል የሚለው አስተሳሰብ በበርካቶች ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ባለፉት ጊዜያት የተደረጉ ጥረቶች ውጤት ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል። ኮሚሽኑ በቅርቡም በትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት እንደሚያካሂድ ገልጸው፥ በተቀሩት ሁሉም ክልሎች፣በአዲስ አበባ ከተማ፣ በድሬዳዋ አሥተዳደር፣ በዳያስፖራው ማኅበረሰብ እና በፌደራል ደረጃ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ተግባራት በስኬት መከናወናቸውንም አክለዋል።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል
Dec 30, 2025 218
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ጠንካራ የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ለዚህም አካታች ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማከናወን፣ የህግ የበላይነት የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት እንዲሁም ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የረጅም ዓመት ታሪክ ውስጥ ብሔራዊ መግባባት አለመስፈን፣ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ አለመፍታት እና ኋላ ቀር የፖለቲካ አመለካከት በሀገረ መንግስቱ ውስጥ የታዩ ስብራቶች መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደትን ማሳካት፣ ምርጫን በተሳካ መንገድ ማካሄድ፣ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የምትሆን ሀገር ለመገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ውጤታማ መሆን የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚፈታ የገለጹት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያን ስብራቶች ከመጠገን አኳያም ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባት ወሣኝ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባት ለመፍጠር ስለሚያግዝ ሁሉም በንቃት መሳተፍ እንዳለበት ጠቅሰው፤ ለግጭት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታትም ትክክለኛ አማራጭ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ሀገራዊ ምክክር ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት መሰረት በሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ብለዋል። የተሳካ ሀገራዊ ምክክር ማከናወን ሁሉም ዜጎች የተግባቡበት የጋራ ሕገ-መንግስት እውን ለማድረግና ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ስለሚረዳ የሁሉንም የነቃ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ነው የተናገሩት። በኢትዮጵያ ኋላቀር የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር፣ አዎንታዊ የሰላም ባህልን ለመገንባት እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብቶቻቸው ሰርተው እንዲለወጡና የበለጸገች ሀገር እንዲገነቡ መሰረት ይጥላል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብና የተሳታፊዎች ልየታ ለማከናወን የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም ከክልሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶች መደረጋቸውን ለምክር ቤቱ ከቀረቡ ሪፖርቶች መገንዘብ እንደሚቻል ተናግረዋል።
የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር የተጀመሩ ተግባራት ስኬታማ እንዲሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ማጎልበት ይጠበቅባቸዋል
Dec 30, 2025 177
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር የተጀመሩ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ሀላፊ ሞገስ ባልቻ ገለጹ። በ"ዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አባበ ለሚገኙ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስልጠና እየተሰጠ ነው። በስልጠና መርሃ ግብሩ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ከተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ሀላፊ ሞገስ ባልቻ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግስት ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው። ለዚህም ጠንካራ ተቋማት አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለተቋማቱ መጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተዋል። የሀገር ግንባታ ሂደት የሚሳካው በኃይልና በግጭት ሳይሆን፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይትና ምክክር በመፍታትና ለሃሳብ የበላይነት ተገዢ በመሆን ነው ብለዋል። መሰል የዲሞክራሲ ልምምድ እንዲጎለብት የሲቪል ማህበራት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። መንግሥት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት መድረክ መመስረቱን ተናግረዋል። ይሄ መድረክ በአዲስ አበባ ደረጃም መመስረቱን አስታውሰው፤ በዚህ መድረክ ላይም በአዲስ አበባ ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ ገልፀዋል። በአዲስ አበባ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ ሚኤሳ ኤሌማ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ስልጠናው በመዲናዋ ያሉ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ይበልጥ ለማጉላት ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመንግሥት እና በድርጅቶች መካከል ይበልጥ ተቀራርቦ ለህዝብ ጥቅም መስራት ሌላው የስልጠናው ዓላማ መሆኑንም አብራርተዋል።
በክልሉ ሰላምን ጠብቆ በማዝለቅ ለልማት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 29, 2025 248
ባሕር ዳር፤ ታሕሳስ 20/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የሰፈነውን ሰላም ጠብቆ በማዝለቅ ለልማት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ። የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ በክልሉ ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማፋጠን በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በየደረጃው የሚገኙ የሚሊሻና የሰላም አስከባሪዎች ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ሰላምን ከማስከበራቸው ጎን ለጎን በልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ሲያከናውኑ እንደቆዩ አንስተዋል። ጠንካራ የሕግ ማስክበር ስራ በማከናወን ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል። ተግባሩን በማጠናከርም የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረትመሰጠቱን ገልጸው፤ በተለይም የክልሉ የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት ዕቅድ ውጤታማ እንዲሆን በጠንካራ አደረጃጀት ሰላም ማስፈን ላይ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም የተቋሙን አደረጃጀት ቀደም ሲል ከነበረበት የጽሕፈት ቤት ደረጃ ወደ ኮሚሽንነት መሸጋገሩን አንስተው፤ የሕግ ማስከበር ሥራውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየተመራ መሆኑን አንስተዋል። የሰላም አማራጭን በመከተል ባለፉት ጊዜያት የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሀድሶ ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ማህበረሰቡ እየተቀላቀሉ መሆኑን አብራርተዋል። የቀሩ ታጣቂዎች ከጥፋታቸው ተመልሰው የበደሉትን ሕዝብ እንዲክሱ አሁንም መንግስት በሆደ ሰፊነት የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል። የሰላም አማራጩን ባልተቀበሉት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል።
የትህነግ ቡድን የመልሶ ማቋቋም ሥራን በማደናቀፍ ተፈናቃዮችን የፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረገ ነው-የስምረት ለዲሞክራሲ ፓርቲ
Dec 28, 2025 343
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 19/2018 (ኢዜአ)፡-የትህነግ ቡድን የመልሶ ማቋቋም ሥራን በማደናቀፍ ተፈናቃዮችን የሴራ ፖለቲካው መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን የስምረት ለዲሞክራሲ ፓርቲ ገለጸ። ሕገ ወጥ ቡድኑ የእርዳታ እህል ለተፈናቃዮች እንዳይደርስ በማድረግ ረሃብ ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን አመልክቷል። የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ አባል ጣዓመ ዓረዶም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፥ በትግራይ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ሕገወጥ ቡድን ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዳይቋቋሙ እንቅፋት ፈጥሯል። ተፈናቃዮችንም የሴራ ፖለቲካው መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሕገወጥ ቡድኑ ለፖለቲካ ትርፍ ሲል በተፈናቃዮች ስም እንደሚነግድ አመልክተው፤ ተፈናቃዮችን በማስፈራራትና ችግር ውስጥ በማስገባት ለርሃብ እየዳረገ መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሕገ ወጥ ቡድኑ ለተፈናቃዮች የሚላከውን እርዳታ በመቀማት ለፖለቲካ ዓላማ እያዋለው እንደሚገኝ አመልክተው፤ መብታቸውን የሚጠይቁትን ደግሞ እያስፈራራ ጉዳት እያደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል በተለይም በመጠለያ ጣቢያዎች እየደረሰ ያለው አስከፊ ችግር ሕገ ወጥ ቡድኑ በሴራ የፈጠረው መሆኑን አብራርተዋል። ይህ ሕገ ወጥ ቡድን የተፈናቃዩቹ ችግር፣ሞትና ስቃይ እንዲቀጥል እያደረገ ነው ያሉት አቶ ጣዓመ፤ በተለይም ወደ ክልሉ የሚገባውን ሰብዓዊ እርዳታና ቁሳቁስ ለተረጂዎች በቀጥታ መድረሱን በተለያየ አካላት ማረጋገጥ እንደሚገባ አመልክተዋል። ሕገ ወጥ ቡድኑ የሴራ ፖለቲካውን ለማራመድ ሲል በጭካኔ በትግራይ ችግር እንዲቀጥል እያደረገ መሆኑንም አንስተዋል። የፌዴራል መንግስት በመጠለያ ጣቢያዎች ለተፈናቃዮች እያደረገ ያለውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን ሀገራዊ ምክክሩ ወርቃማ ዕድል ነው
Dec 28, 2025 308
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 19/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን የሀገራዊ ምክክሩ ያስገኘውን ወርቃማ ዕድል ሁሉም ዜጋ ሊጠቀምበት እንደሚገባ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን የማደራጀትና ግብዓቶችን የማሰባሰብ ተግባራት በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ማሳወቁ ይታወሳል። የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አህመድ ሁሴን፤ ኢትዮጵያዊያን ምክክር በማድረግ በጋራ አጀንዳዎች ላይ መግባባት ባለመፍጠራቸው ሀገር ዋጋ ስትከፍል መቆየቷን ገልጸዋል። በዚህም መነሻነት ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት ሲንከባለሉ በቆዩ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ወርቃማ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያም በሃሳብ የበላይነት የተመሠረተ ሀገራዊ ምክክር በማካሄድ ብሔራዊ መግባባትን ማጠናከር የሚያስችል የዳበረ የዴሞክራሲ ሥርዓትና የፖለቲካ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሀገራዊ ምክክር አሳታፊ፣ አካታችና ተዓማኒነት ለማስጠበቅ በተከናወኑ የቅድመ ጉባኤ ምክክር ሂደቶች ላይ አዎንታዊ ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። ብሄራዊ መግባባትን ለማጠናከርና አንድነትን ለማጽናት ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ዕድል መሆኑንም አመልክተዋል። በቀጣይ ብሔራዊ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የተፈጠረውን የሀገራዊ ምክክር ዕድል ሁሉም ዜጋ ሊጠቀምበት እንደሚገባ አስረድተዋል። የተርካንፊ ሰስተነብል ዴቨሎፕመንት መስራችና ዳይሬክተር ወርቅነሽ ቤጊ፤ በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሂደት የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ሴቶች በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ብሔራዊ መግባባት የሚሹ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ተናግረዋል። የዋይቡንቱ ዪዝ ፒስ ቢወልዲንግ አሊያንስ ፀሐፊ ሲሳይ ታረቀኝ፥ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደትም የወጣቶችን የነቃ ተሳትፎ የሚያረጋግጡ ተግባራትን እያከናወኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። በቀጣይም ለዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የመደመር መንግስት እሳቤን በመተግበር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቷል
Dec 27, 2025 296
ደብረ ማርቆስ/ገንዳ ውሃ/ወልዲያ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-የመደመር መንግስት እሳቤን በመተግበር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማጠናከር ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ። በደብረ ማርቆስ፣ ገንዳ ውሃና በወልዲያ ከተሞች "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል ሃሳብ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉባቸው የውይይት መድረኮች ተካሂደዋል። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በተካሄደ መድረክ ላይ የአስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ እንደገለጹት፤ የመደመር መንግስት በወል ትርክት ላይ የተመሰረተ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት እየሰራ ነው። ለዚህም የቀደመ መልካም እሴቶች ላይ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት ግብ ተይዞ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማ አስተዳደሩ በመንገድ፣ በኢንዱስትሪ፣ በሃይል አቅርቦትና ሌሎች መሰል መሰረተ ልማቶች ማተኮሩንም ገልጸዋል። ከልማት ሥራዎች በተጓዳኝ በአካባቢው ሰላምን አጠናክሮ ለማስቀጠል ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ነው ያስረዱት። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ህዝብን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአካባቢን ሀብት ለይቶ ማልማት ከተቻለ ድህነትን ማሸነፍ እንደሚቻል ትምህርት የተገኘባቸው ናቸው ብለዋል። በመደመር መንግስት በልማትና በመልካም አስተዳደር የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ሥራዎች ይጠናከራሉ ያሉት ደግሞ በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ የተገኙት የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ ናቸው። በዞኑ ያሉትን ፀጋዎች አልምቶ ለህዝብ ጥቅም ለማዋል ሰላምን ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ለዚህም በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ አብዱልከሪም ሙሀመድ በበኩላቸው፤ በመደመር መንግስት እሳቤ በከተማዋ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት እየተሰራ ነው። የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በአገር አቀፍ ደረጃ በስኬት የተጠናቀቁ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የመንግስትን የልማት ቁርጠኝነት ያሳያሉ። የመደመር መንግስት እሳቤዎችን ለማሳካት በሰላምና ልማት ግንባታ ላይ ህዝብን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ናቸው። ህዝቡም ሠላምና ልማትን የሚያደናቅፉ አካላትን በአደባባይ ጭምር ማውገዙን አስታውሰው ይህም ተጠናክሮ መጠቀል እንዳለበት አሳስበዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በአካባቢው የሰፈነው ሠላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡ አድርገዋል። በየከተሞቹ በተካሄደ የውይይት መድረክ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
በመሪዎች መካከል የተደረጉ ስምምነቶችን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው
Dec 31, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያና ህንድ መሪዎች መካከል የተደረጉ ስምምነቶችን ተግባራዊ ለማድረግ እና የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂክ አጋርነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ ገለፁ። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ማደጉ ከኢኮኖሚና ንግድ ባለፈ ያላቸውን የትብብር አድማስ የሚያሰፋ መሆኑንም ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለፁት፤ኢትዮጵያና ህንድ ለረጅም ዘመናት የዘለቀ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው። ኢትዮጵያ በህንድ የባህል ማዕከል ያላት ብቸኛ አፍሪካዊት ሀገር መሆኗን አንስተው፤ የኢትዮጵያን ባህል በህንድ የበለጠ ለማስተዋወቅ እንደሚሰራም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት ከ40 በላይ በረራ ወደ ህንድ እንደሚያደርግ የገለጹት አምባሳደሩ ተቋሙን የኢትዮጵያ የባህል አምባሳደር ሲሉ አሞካሽተውታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ናሪንድራ ሞዲ ጉብኝትን ተከትሎ የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ማደጉንም አስታውሰዋል። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ማደጉ ከኢኮኖሚና ንግድ ባለፈ የትብብር አድማስን የሚያሰፋ መሆኑን ጠቁመዋል። ጉብኝቱን ተከትሎ ሀገራቱ በጉምሩክ፣ በሰላም ማስከበር፣ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዳታ ማዕከል መገንባትን ጨምሮ የተለያዩ ስምምነቶች መፈራረማቸውንም አስታውሰዋል። የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ማደግ የደቡብ ለደቡብ ትብብርን የሚያጠናክርና ሀገራቱ ያላቸውን ዓለም አቀፍ አጋርነት የሚያጎለብት መሆኑን አስረድተዋል። በህንድ የትምህርት እድል የሚያገኙ ኢትዮጵያውያንን ቁጥር በእጥፍ ለማሳደግ ስምምነት ላይ መደረሱንም አንስተዋል። ሀገራቱ በጋራ ለመስራት የተስማሙባቸውን ተግባራት ለማስፈፀምና ስትራቴጂክ አጋርነቱን ለማጠናከር የሚያስችል ፍኖተ ካርታ እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግረዋል።
እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል-ኮሚሽኑ
Dec 30, 2025 218
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 21/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመ ጀምሮ ባከናወናቸው ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ሀገራዊ ምክክሩን ለመምራት ገለልተኛ ሆኖ መዋቀሩን ያስገነዘቡት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቃል አቀባይ ጥበቡ ታደሰ፤ እስካሁን ስኬታማ ተግባራት ማከናወኑን ለኢዜአ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ባለድርሻ አካላት ተለይተው በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ በማድረግ ረገድ በርካታ ውጤቶች የተገኙባቸው ሥራዎች ተሠርተዋል ብለዋል። አጀንዳ የተሰበሰበበት መንገድ በርካቶች የተስተናገዱባቸው መድረኮች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህም የዴሞክራሲ ልምምድን በማሳደግ የምክክር ሂደት እንዲዳብር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። የምክክር ሂደቱ የኢትዮጵያውያን እንዲሆንና ባለድርሻ አካላት የሂደቱ ባለቤት እንዲሆኑ የተሠሩ ሥራዎችም ውጤት የተገኘባቸው መሆናቸውን ነው ያስገነዘቡት። በግልጽና ገለልተኛ አሠራር አካታችና አሳታፊ በሆነ መንገድ ተሳታፊዎችን መለየት መቻሉ ከተገኙ ውጤቶች መካከል መሆኑንም ጠቁመዋል። በውክልና የመሳተፍ ልምምዶችን፣ዴሞክራሲያዊ ባሕርይን የማምጣቱ ጉዳይም ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው መሆኑን አመላክተው፤ 93 በመቶ የኢትዮጵያ ወረዳዎችን በምክክር ሂደቱ ማሳተፍ መቻሉን አመላክተዋል። በሕዝቡ፣በባለድርሻ አካላት፣ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡም ጭምር ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ተቀባይነት እንዲኖረው የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት መሆኑንም ነው ያረጋገጡት። በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት እንደተጠበቁ ሆነው በሂደት ከኃይል አማራጭ ይልቅ ምክክር የተሻለ ውጤታማ ያደርጋል የሚለው አስተሳሰብ በበርካቶች ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ባለፉት ጊዜያት የተደረጉ ጥረቶች ውጤት ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል። ኮሚሽኑ በቅርቡም በትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት እንደሚያካሂድ ገልጸው፥ በተቀሩት ሁሉም ክልሎች፣በአዲስ አበባ ከተማ፣ በድሬዳዋ አሥተዳደር፣ በዳያስፖራው ማኅበረሰብ እና በፌደራል ደረጃ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ተግባራት በስኬት መከናወናቸውንም አክለዋል።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል
Dec 30, 2025 218
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት መሠረት የሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ጠንካራ የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ለዚህም አካታች ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማከናወን፣ የህግ የበላይነት የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት እንዲሁም ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የረጅም ዓመት ታሪክ ውስጥ ብሔራዊ መግባባት አለመስፈን፣ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ አለመፍታት እና ኋላ ቀር የፖለቲካ አመለካከት በሀገረ መንግስቱ ውስጥ የታዩ ስብራቶች መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደትን ማሳካት፣ ምርጫን በተሳካ መንገድ ማካሄድ፣ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የምትሆን ሀገር ለመገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ውጤታማ መሆን የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚፈታ የገለጹት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያን ስብራቶች ከመጠገን አኳያም ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባት ወሣኝ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባት ለመፍጠር ስለሚያግዝ ሁሉም በንቃት መሳተፍ እንዳለበት ጠቅሰው፤ ለግጭት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታትም ትክክለኛ አማራጭ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ሀገራዊ ምክክር ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት መሰረት በሚጥልበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ብለዋል። የተሳካ ሀገራዊ ምክክር ማከናወን ሁሉም ዜጎች የተግባቡበት የጋራ ሕገ-መንግስት እውን ለማድረግና ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ስለሚረዳ የሁሉንም የነቃ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ነው የተናገሩት። በኢትዮጵያ ኋላቀር የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር፣ አዎንታዊ የሰላም ባህልን ለመገንባት እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብቶቻቸው ሰርተው እንዲለወጡና የበለጸገች ሀገር እንዲገነቡ መሰረት ይጥላል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብና የተሳታፊዎች ልየታ ለማከናወን የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም ከክልሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶች መደረጋቸውን ለምክር ቤቱ ከቀረቡ ሪፖርቶች መገንዘብ እንደሚቻል ተናግረዋል።
የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር የተጀመሩ ተግባራት ስኬታማ እንዲሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ማጎልበት ይጠበቅባቸዋል
Dec 30, 2025 177
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር የተጀመሩ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ሀላፊ ሞገስ ባልቻ ገለጹ። በ"ዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አባበ ለሚገኙ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስልጠና እየተሰጠ ነው። በስልጠና መርሃ ግብሩ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ከተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ሀላፊ ሞገስ ባልቻ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግስት ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው። ለዚህም ጠንካራ ተቋማት አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለተቋማቱ መጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተዋል። የሀገር ግንባታ ሂደት የሚሳካው በኃይልና በግጭት ሳይሆን፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይትና ምክክር በመፍታትና ለሃሳብ የበላይነት ተገዢ በመሆን ነው ብለዋል። መሰል የዲሞክራሲ ልምምድ እንዲጎለብት የሲቪል ማህበራት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። መንግሥት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት መድረክ መመስረቱን ተናግረዋል። ይሄ መድረክ በአዲስ አበባ ደረጃም መመስረቱን አስታውሰው፤ በዚህ መድረክ ላይም በአዲስ አበባ ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ ገልፀዋል። በአዲስ አበባ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ ሚኤሳ ኤሌማ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ስልጠናው በመዲናዋ ያሉ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚናቸውን ይበልጥ ለማጉላት ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመንግሥት እና በድርጅቶች መካከል ይበልጥ ተቀራርቦ ለህዝብ ጥቅም መስራት ሌላው የስልጠናው ዓላማ መሆኑንም አብራርተዋል።
በክልሉ ሰላምን ጠብቆ በማዝለቅ ለልማት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 29, 2025 248
ባሕር ዳር፤ ታሕሳስ 20/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የሰፈነውን ሰላም ጠብቆ በማዝለቅ ለልማት ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ። የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ በክልሉ ሰላምን በማፅናት ልማትን ለማፋጠን በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በየደረጃው የሚገኙ የሚሊሻና የሰላም አስከባሪዎች ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ሰላምን ከማስከበራቸው ጎን ለጎን በልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ሲያከናውኑ እንደቆዩ አንስተዋል። ጠንካራ የሕግ ማስክበር ስራ በማከናወን ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል። ተግባሩን በማጠናከርም የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረትመሰጠቱን ገልጸው፤ በተለይም የክልሉ የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት ዕቅድ ውጤታማ እንዲሆን በጠንካራ አደረጃጀት ሰላም ማስፈን ላይ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም የተቋሙን አደረጃጀት ቀደም ሲል ከነበረበት የጽሕፈት ቤት ደረጃ ወደ ኮሚሽንነት መሸጋገሩን አንስተው፤ የሕግ ማስከበር ሥራውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየተመራ መሆኑን አንስተዋል። የሰላም አማራጭን በመከተል ባለፉት ጊዜያት የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሀድሶ ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ማህበረሰቡ እየተቀላቀሉ መሆኑን አብራርተዋል። የቀሩ ታጣቂዎች ከጥፋታቸው ተመልሰው የበደሉትን ሕዝብ እንዲክሱ አሁንም መንግስት በሆደ ሰፊነት የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል። የሰላም አማራጩን ባልተቀበሉት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል።
የትህነግ ቡድን የመልሶ ማቋቋም ሥራን በማደናቀፍ ተፈናቃዮችን የፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረገ ነው-የስምረት ለዲሞክራሲ ፓርቲ
Dec 28, 2025 343
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 19/2018 (ኢዜአ)፡-የትህነግ ቡድን የመልሶ ማቋቋም ሥራን በማደናቀፍ ተፈናቃዮችን የሴራ ፖለቲካው መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን የስምረት ለዲሞክራሲ ፓርቲ ገለጸ። ሕገ ወጥ ቡድኑ የእርዳታ እህል ለተፈናቃዮች እንዳይደርስ በማድረግ ረሃብ ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን አመልክቷል። የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ አባል ጣዓመ ዓረዶም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፥ በትግራይ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ሕገወጥ ቡድን ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዳይቋቋሙ እንቅፋት ፈጥሯል። ተፈናቃዮችንም የሴራ ፖለቲካው መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሕገወጥ ቡድኑ ለፖለቲካ ትርፍ ሲል በተፈናቃዮች ስም እንደሚነግድ አመልክተው፤ ተፈናቃዮችን በማስፈራራትና ችግር ውስጥ በማስገባት ለርሃብ እየዳረገ መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሕገ ወጥ ቡድኑ ለተፈናቃዮች የሚላከውን እርዳታ በመቀማት ለፖለቲካ ዓላማ እያዋለው እንደሚገኝ አመልክተው፤ መብታቸውን የሚጠይቁትን ደግሞ እያስፈራራ ጉዳት እያደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል በተለይም በመጠለያ ጣቢያዎች እየደረሰ ያለው አስከፊ ችግር ሕገ ወጥ ቡድኑ በሴራ የፈጠረው መሆኑን አብራርተዋል። ይህ ሕገ ወጥ ቡድን የተፈናቃዩቹ ችግር፣ሞትና ስቃይ እንዲቀጥል እያደረገ ነው ያሉት አቶ ጣዓመ፤ በተለይም ወደ ክልሉ የሚገባውን ሰብዓዊ እርዳታና ቁሳቁስ ለተረጂዎች በቀጥታ መድረሱን በተለያየ አካላት ማረጋገጥ እንደሚገባ አመልክተዋል። ሕገ ወጥ ቡድኑ የሴራ ፖለቲካውን ለማራመድ ሲል በጭካኔ በትግራይ ችግር እንዲቀጥል እያደረገ መሆኑንም አንስተዋል። የፌዴራል መንግስት በመጠለያ ጣቢያዎች ለተፈናቃዮች እያደረገ ያለውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን ሀገራዊ ምክክሩ ወርቃማ ዕድል ነው
Dec 28, 2025 308
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 19/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን የሀገራዊ ምክክሩ ያስገኘውን ወርቃማ ዕድል ሁሉም ዜጋ ሊጠቀምበት እንደሚገባ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን የማደራጀትና ግብዓቶችን የማሰባሰብ ተግባራት በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ማሳወቁ ይታወሳል። የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አህመድ ሁሴን፤ ኢትዮጵያዊያን ምክክር በማድረግ በጋራ አጀንዳዎች ላይ መግባባት ባለመፍጠራቸው ሀገር ዋጋ ስትከፍል መቆየቷን ገልጸዋል። በዚህም መነሻነት ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት ሲንከባለሉ በቆዩ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ወርቃማ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያም በሃሳብ የበላይነት የተመሠረተ ሀገራዊ ምክክር በማካሄድ ብሔራዊ መግባባትን ማጠናከር የሚያስችል የዳበረ የዴሞክራሲ ሥርዓትና የፖለቲካ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሀገራዊ ምክክር አሳታፊ፣ አካታችና ተዓማኒነት ለማስጠበቅ በተከናወኑ የቅድመ ጉባኤ ምክክር ሂደቶች ላይ አዎንታዊ ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። ብሄራዊ መግባባትን ለማጠናከርና አንድነትን ለማጽናት ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ዕድል መሆኑንም አመልክተዋል። በቀጣይ ብሔራዊ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የተፈጠረውን የሀገራዊ ምክክር ዕድል ሁሉም ዜጋ ሊጠቀምበት እንደሚገባ አስረድተዋል። የተርካንፊ ሰስተነብል ዴቨሎፕመንት መስራችና ዳይሬክተር ወርቅነሽ ቤጊ፤ በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሂደት የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ሴቶች በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ብሔራዊ መግባባት የሚሹ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን ተናግረዋል። የዋይቡንቱ ዪዝ ፒስ ቢወልዲንግ አሊያንስ ፀሐፊ ሲሳይ ታረቀኝ፥ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደትም የወጣቶችን የነቃ ተሳትፎ የሚያረጋግጡ ተግባራትን እያከናወኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። በቀጣይም ለዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የመደመር መንግስት እሳቤን በመተግበር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቷል
Dec 27, 2025 296
ደብረ ማርቆስ/ገንዳ ውሃ/ወልዲያ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-የመደመር መንግስት እሳቤን በመተግበር የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማጠናከር ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ። በደብረ ማርቆስ፣ ገንዳ ውሃና በወልዲያ ከተሞች "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል ሃሳብ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉባቸው የውይይት መድረኮች ተካሂደዋል። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በተካሄደ መድረክ ላይ የአስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ እንደገለጹት፤ የመደመር መንግስት በወል ትርክት ላይ የተመሰረተ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት እየሰራ ነው። ለዚህም የቀደመ መልካም እሴቶች ላይ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት ግብ ተይዞ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማ አስተዳደሩ በመንገድ፣ በኢንዱስትሪ፣ በሃይል አቅርቦትና ሌሎች መሰል መሰረተ ልማቶች ማተኮሩንም ገልጸዋል። ከልማት ሥራዎች በተጓዳኝ በአካባቢው ሰላምን አጠናክሮ ለማስቀጠል ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ነው ያስረዱት። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ህዝብን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአካባቢን ሀብት ለይቶ ማልማት ከተቻለ ድህነትን ማሸነፍ እንደሚቻል ትምህርት የተገኘባቸው ናቸው ብለዋል። በመደመር መንግስት በልማትና በመልካም አስተዳደር የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ሥራዎች ይጠናከራሉ ያሉት ደግሞ በገንዳ ውሃ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ የተገኙት የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ ናቸው። በዞኑ ያሉትን ፀጋዎች አልምቶ ለህዝብ ጥቅም ለማዋል ሰላምን ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ለዚህም በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ አብዱልከሪም ሙሀመድ በበኩላቸው፤ በመደመር መንግስት እሳቤ በከተማዋ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት እየተሰራ ነው። የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በአገር አቀፍ ደረጃ በስኬት የተጠናቀቁ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የመንግስትን የልማት ቁርጠኝነት ያሳያሉ። የመደመር መንግስት እሳቤዎችን ለማሳካት በሰላምና ልማት ግንባታ ላይ ህዝብን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ናቸው። ህዝቡም ሠላምና ልማትን የሚያደናቅፉ አካላትን በአደባባይ ጭምር ማውገዙን አስታውሰው ይህም ተጠናክሮ መጠቀል እንዳለበት አሳስበዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በአካባቢው የሰፈነው ሠላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡ አድርገዋል። በየከተሞቹ በተካሄደ የውይይት መድረክ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ማህበራዊ
በአማራ ክልል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎትን ማቀላጠፍ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Dec 31, 2025 5
ደብረ ማርቆስ፤ ታህሳስ 22/2018 (ኢዜአ)፡ -በአማራ ክልል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎትን ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ የዲጅታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማጎልበት ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በደብረማርቆስ ከተማ አካሄዷል። የክልሉ ሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ኃላፊ ማዓዛ በዛብህ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የክልሉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን በጠራ መረጃ ለማስደገፍ እየተሰራ ነው። ለዚህም በ8 "ሪጅኦ ፖሊታንት" ከተሞች በ204 ጣቢያዎች የተጀመረውን ሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ዲጅታላይዝድ በማድረግ ባለፉት 5 ወራት ብቻ ከ450 ሺህ በላይ የሞት፣ ጋብቻ፣ ፍቺና ልደት ኩነትን መመዝገብ መቻሉን አስረድተዋል። የአሰራሩ ዲጂታላይዝ መደረጉም ከዚህ ቀደም በዓመት ለቅጻቅጽ ግዥ ይወጣ የነበረን ከ3 ሚሊየን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ብለዋል። በመጀመሪያው ዙር የተገኘውን ተሞክሮ በማስፋት የ2ኛውን ዙር የዲጅታል ምዝገባ ስርዓት አጠናክሮ ለማስቀጠል የዛሬው መድረክ መከናወኑንም ገልጸዋል። የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ በበኩላቸው፤ ዲጅታል ኢትዮጵያ ቦዞኑ በአገልግሎት አሰጣጥ የነበረውን የተንዛዛ አሰራር መቀነስ አስችሏል ብለዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም የምዝገባ ሂደቱን በዲጅታል በማከናወን ግልጽና ታማኒነት ያለው መረጃን ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ለማድረግ አቅም የሚፈጥር ነው ሲሉ ተናግረዋል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ፤ የከተማ አስተዳደሩ በገቢዎች፣ በሲቪልና በቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት፣ በካዳስተርና ሌሎች የስራ መስኮች የዲጅታል አገልግሎት እየተገበረ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የሀረር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ የተቀናጀ ርብርብ እየተደረገ ነው
Dec 31, 2025 20
ሀረር፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በሀረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ የተቀናጀ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ በሀረር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከጉብኝቱ በኋላ እንደተናገሩትም የሀረር ከተማን ድምቀትና ውበት ይበልጥ የሚያጎናጽፉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል። ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ እንዲሁም ለመጪው ትውልድ መሰረት የሚጥሉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው የኮሪደር ልማት ስራው አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ዙሪያ የቅርሱን ይዘት በጠበቀ መልኩ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ቅርስን ጠብቆ ከማቆየት ባለፈ ትውልዱ በታሪክ እንዲወሳ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸው የተጀመሩ የልማት ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የተከናወኑና በሂደት ላይ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች የተሽከርካሪና የእግረኛ መንገዶች፣ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ ፋውንቴኖች፣ የፍሳሽ ማስወገጃዎች፣ የአረንጓዴ ስፍራና የመንገድ ዳር መብራትን ያካተቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ የተቀናጀ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በሚሰሩ ስራዎች ህዝቡ እያደረገ የሚገኘው ትብብርና ድጋፍ ስራውን ከማገዝ ባለፈ ለበለጠ ውጤት የሚያነሳሳ መሆኑንም አስረድተዋል። በየአካባቢው እየተከናወኑ ለሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች መሰረተ ልማት እንዲሟላ ከማስቻል ባሻገር ህገ ወጥነትን ለመከላከል ጭምር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
በሀገራዊ ወግና ባህል የተቃኘ፣ ከዓለም እኩል መራመድ የሚያስችል ትምህርትና ሥልጣኔን ለማጠናከር በትኩረት ይሰራል
Dec 31, 2025 26
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ወግና ባህል የተቃኘ፣ ከዓለም እኩል መራመድ የሚያስችል ትምህርት፣ ቴክኖሎጂና ሥልጣኔ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ይገኛል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በ75 ዓመታት ጉዞው ከ300 ሺህ በላይ ምሩቃንን በማፍራት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ዘርፎች ላይ የራሱን አሻራ አሳርፏል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዩኒቨርሲቲው ከሀገር መሪዎች እስከ ዓለም አቀፍ ተመራማሪዎችን ያፈራ የሀገር ባለውለታ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ የተሳለጠ የውጭና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መንገድ አሳይቷል፤ ለግብርናና አካባቢ ጥበቃ ስራዎች ሀሳብ አዋጥቷል፣ ለትምህርትና ስልጠና ስርዓት መሻሻል መሰረት ጥሏል ብለዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው 75ኛ ዓመት በዓል ሲከበር ስራዎችን ለመዘከርና ታረክ ለመንገር ብቻ አይደለም ያሉት ሳሙኤል (ዶ/ር)፤ ለሀገራዊ ብልጽግና አጋዥ ሀሳቦችን ለማለም ጭምር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ፤ የ75ኛ ዓመት ምስረታ በዓልና የራስ ገዝነት አስተዳደር የተገናኙበትን የታሪክ ግጥምጥሞሽም የቀጣይ ሥራዎችን በፍጥነትና በጥራት ለመስራት መልካም ዕድል የፈጠረ ብለውታል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በራስ ገዝነት ያገኘውን ወርቃማ ዕድል በመጠቀም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ኃላፊነቱን ይወጣል ብለዋል፡፡ በቀጣይ ዩኒቨርሲቲው ያገኘውን የራስ ገዝነት ዕድልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመጥርና ለኢትዮጵያና ህዝቦች ዕድገት ገንቢ ሚና የሚወጣ ተቋም እንዲሆን ያስችለዋል ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ በሀገራዊ ወግና ባህል የተቃኘ፣ ከዓለም እኩል መራመድ የሚያስችል ትምህርት፣ ቴክኖሎጂና ሥልጣኔ ሊኖራት ይገባል ያሉት ሳሙኤል (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ለዚህ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የቀጣዩ ዘመን የመወዳደሪያ መድረክ መሆኑን ገልጸው፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ፕሮግራሙን በሶስተኛ ዲግሪ ደረጃ ማስተማር ጀምሯል ብለዋል፡፡ ይሄውም የመንግስት የፖሊሲ አቅጣጫዎች ማሳካትና ኢትዮጵያ በነባራዊው ዓለም ተወዳዳሪ የምትሆንበትን አውድ እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለመለወጥ በምታደርገው ጥረት በጥናትና ምርምር የታገዘ ድጋፍ በማድረግ ኃላፊነቱን መወጣቱን ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ጥልቅ ንባቡን እና የሀገር ፍቅሩን በስራዎቹ የገለጠ የጥበብ ሰው - ያየህይራድ አላምረው
Dec 31, 2025 52
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ የሁለገቡ የጥበብ ሰው ያየህይራድ አላምረው የመፃሕፍት፣ መዛግብትና የጥበብ ስራ ስብስቦች ለኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ተበርክተዋል። የተበረከቱ የመዛግብት፣ የመጻሕፍትና የጥብብ ስራ ስብስቦች ‘የአርቲስት ያየህይራድ አላምረው መዘክርና የስብስቦቹ ቤተ መፃሕፍት’ በሚል ስያሜ በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ውስጥ ተደራጅተው ክፍት ተደርገዋል። ሀገር ተኮር በሆኑ የዘፈን ግጥሞችና ዜማዎች ደራሲነቱ እንዲሁም በፕሮዲዩሰርነት የሚታወቀው ያየህይራድ አላምረው ባሳለፍነው ዓመት ታህሳስ ወር ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው። በንባብ ወዳድነቱና መዛግብት ሰብሳቢነቱ የሚታወቀው አርቲስቱ በሕይወት ዘመኑ ያሰባሰባቸውን ከ5 ሺህ በላይ መፃሕፍት፣ መዛግብትና የጥበብ ስራ ውጤት የሆኑ ስብስቦች በቤተሰቦቹ በኩል ለኢትዮጵያ ቤተ መፃሕፍት አገልግሎት ተበርክተዋል። በኢትዮጵያ የቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት የተደራጀው የያየህይራድ ስብስቦች ቤተ መፃሕፍት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ(ረ/ፕ)ን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የኪነ ጥበብ ሰዎች፣ የአርቲስቱ ቤተሰቦችና ወዳጆቹ በተገኙበት ዛሬ ይፋ ተደርጓል። ሚኒስትር ዴኤታው ነብዩ ባዬ በዚህ ወቅት እንዳሉት ያየህይራድ አላምረው በንባብ የተገራና የለሰለሰ፣ አስተዋይ እና ፈገግታ የማይለየው የመልካም ስብዕና ባለቤት የጥበብ ሰው ነበር። ያየህይራድ በጥልቅ አንባቢነቱና ከቤተሰብ የወረሰውን የኢትዮጵያ አፍቃሪነቱን በጥበብ ስራዎቹ የገለጠ ድንቅ ባለሙያ እንደሆነ ገልፀዋል። በሕይወት ዘመኑ ያሰባሰባቸው መፃሕፍት እና ሌሎች ስብስቦች ለትውልድ እንዲተርፉ ለአንጋፋው ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃሕፍት አገልግሎት ተደራጅተው እንዲያቀርቡ ያደረጉ አካላትንም አመስግነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር እና የያየይራድ የቅርብ ጓደኛ የሆኑት ጌታቸው ረዳ ያየህይራድ አላምረው ማንበብ የሚወድ፣ ሃሳቡን በቀላሉ መግለጽ የሚችል እና ለሁሉም ጓደኛ መሆን የሚችል የዋህ ሰው እንደነበር ተናግረዋል። የአርቲስቱ የመፃሕፍትና የጥበብ ስራዎች ውጤቶች በዚህ መልኩ ተደራጀተው ለታሪክ መቀመጣቸው ትልቅ ቁምነገር ስለመሆኑም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰርፀፍሬ ስብሃት በበኩላቸው ያየህይራድ ብዙ ያወቀ ዳሩ በስራዎቹ ጥልቀት ልክ በቅጡ ያልታወቀና ያልተነገረለት የጥበብ ሰው መሆኑን ገልጸዋል። ለአገልግሎቱ የተበረከቱ ስብሰቦች ይዘትና አይነት እጅግ አስደናቂ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ያየህይራድ አንባቢነትና የሀገር ፍቅር ለኪነ ጥበብ ሰዎች በተምሳሌትነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። አርቲስቱ በጥበብ ስራዎቹ ያሳየውን የሃሳብ ገለፃ፣ የቃላት አጠቃቀምና የመልዕክቱን ጥልቀት አንስተዋል። ‘ከይቺ ናት ሀገሬ እስከ ቁሜ ልመርቅሽ’ አያሌ የኢትዮጵያ ዕውቅ ሙዚቀኞች ተወዳጅ ዘፈኖች የያየህይራድ አላምረው አሻራዎች ማሳያ እንደሆኑ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በያየህይራድ ‘አንጀት አርስ’ ብዕር መገለጧን ጠቅሰው፤ አሁን ደግሞ የያየህይራድ ስብስቦች በአገልግሎቱ ውስጥ ተደራጅተው ለኢትዮጵያ ተገልጠዋል ነው ያሉት። አንጋፋው የኢትዮጵያ ቤተ መዛግበትና ቤተ መፃሕፍት አገልግሎት ኢትዮጵያን ለማወቅ እና መዛግብትን ለትውልድ ለማሻገር ሁናኘ ስፍራ መሆኑን በመጥቅስ የጥበብ ሰዎችም ይህን አርዓያነት እንዲከተሉ ጠይቀዋል። በመድረኩ ላይ ሃሳባቸውን የሰጡት የአርቲስቱ ቤተሰቦችና ወዳጆችም ያየህይራድ በሀገር ፍቅር ስሜት፣ በጥልቅ አንባቢነትና በጥበብ ስራዎች ረቂቅነቱን ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
የክልሉን እምቅ የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ለማስደገፍ ትኩረት ተድርጓል
Dec 31, 2025 28
ዲላ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ያለውን እምቅ የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ለማስደገፍ ትኩረት መደረጉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ልማት አቅም ልየታ ላይ ያተኮረ መርሃ ግብር በዲላ ከተማ የተካሄደ ሲሆን ከውይይት መድረኩ በኋላ በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ ቱማታ ጭራቻ ቀበሌ 60 ሄክታር የቡና ኩታ ገጠም እርሻ የመስክ ምልከታ ተደርጓል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በማጠቃለያው እንዳሉት የክልሉን እምቅ የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀም በጥናትና ምርምር ማስደገፍ ወሳኝ ነው። በተለይ በክልሉ ያለውን ሰፊ መሬትና የውኃ ሀብት ከቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ወደ ተግባር ለመለወጥ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል። ክልሉ በግብርና ልማት ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ አምራች እንዲሆን ጥናትና ምርምርን መሰረት ያደረገ ስራ እንደሚሰራ አመልክተው የዛሬው መድረክም ይህንኑ ለማጠናከር የተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ የቀረቡ ምክረ ሀሳቦችን በመተግበር ከፍተኛ ምርት ለማምረት የዘርፉ ባለድርሻ አካላትና አመራሩ በቅንጅት መስራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለግብርና ልማት ምቹ የሆነ ተፈጥሮ የታደለ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ናቸው። የግብርና አቅሞችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ የአርሶ እና አርብቶ አደሩን ህይወት በመለወጥ ሀገርን ማሳደግ እንደሚቻልም ጠቅሰዋል። በተለይም የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም በኩል በክልሉ የሚስተዋለውን ውስንነት በመቅረፍ የግብርና ሽግግርን ማፋጠን እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በእውቀት ላይ በመመስረት የሚከናወን የግብርና ልማት ስራ የኢትዮጵያን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሳካት ዋሳኝ ሚና እንደሚጫወትም አክለዋል።
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዓለም አቀፍ የግብይት ተወዳዳሪነትን በማስፋት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይጠበቅበታል
Dec 31, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዓለም አቀፍ የግብይት ተወዳዳሪነትን በማስፋት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚጠበቅበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ፣ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው ከ2014 እስከ 2016 ዓ.ም ድረስ ያለውን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የምርት ቅበላ፣ ክምችና የግብይት ስርዓት ላይ የተካሔደ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ላይ ተወያይቷል። በክዋኔ ኦዲት እንደክፍተት ከታዩ ጉዳዮች መካከል የምርት አቀባበል ሂደት እና ዘመናዊ የግብይት አሰራር መፍጠር ላይ የተነሱ ጉድለቶች ተጠቃሽ ናቸው። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ አራሬ ሞሲሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ምርት ገበያው በክዋኔ ኦዲት ግኝት የተቀመጡ ክፍተቶችን በማስተካከል የተሰጠውን ኃላፊነት በሚገባ መወጣት ይኖርበታል። በተለይም በመጋዘን ኪራይና ግንባታ ላይ በቋሚ ኮሚቴው የተሰጠውን የክዋኔ ኦዲት አስተያየት በማስተካከል የአርሶ አደሩንና የሀገርን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባው አስገንዝበዋል። የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተነደፈው የምርት ቅበላ፣ ግብይትና ክምችት የድርጊት መርሃ ግብር ተፈፃሚነትም በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሀኪም ሙሉ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በምርት ገበያው የተስተዋሉ የኦዲት ግኝቶች ላይ የተቀናጀ የእርምት እርምጃ ለመውሰድ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የሚያሻሽል ወቅታዊ መረጃዎችን በመስጠት ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ግኝት ጭምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እየበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ቀደም ብሎ በቋሚ ኮሚቴው የተሰጡ የኦዲት ግኝት አስተያየቶችን ተከትሎ በተወሰዱ እርምጃዎች በሰው ሃብት ልማትና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ስኬታማ ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሰረት ዳምጤ፤ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በመጋዘን አያያዝና ዘመናዊ ግብይት አሰራሮች ላይ የተሰጡትን የኦዲት ግኝቶች ለማስተካከል በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በቀጣይም በምርት ገበያው የክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ላይ አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ ምርት በዓለም አቀፍ ገበያ በማቅረብ ተወዳዳሪነትን ማሻሻል እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መርጋ በይሳ በበኩላቸው፤ ቋሚ ኮሚቴው በምርት ገበያው በሰጠው የክዋኔ ኦዲት ክፍተት አስተያየት ላይ የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ ነው ብለዋል። በዚህም ነባርና አዳዲስ ምርቶችን ከምርት ገበያው ጋር በማሰናሰል አርሶ አደሮች በቀጥታ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አሰራር የማስፋት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በቀጣይም በዋና ኦዲተር የተመላከቱ የክዋኔ ኦዲት ግኝቶችን በማስተካከል ዓለም አቀፍ የምርት ገበያ ተወዳዳሪነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ ከቀጣናው ሀገራት ጋር የምታከናውናቸው ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት ለጋራ ልማትና ዕድገት ወሳኝ ሚና አላቸው
Dec 31, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከቀጣናው ሀገራት ጋር የምታከናውናቸው ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት ለጋራ ልማትና ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። ምሁራኑ ቀጣናዊ ትስስር መፈጠር የንግድ ፍሰቱን ከማሳለጥ ባለፈ ለዘላቂ ሰላምና ለሁለንተናዊ እድገት መሰረት በመሆኑ በጋራ የመልማት አስፈላጊነትን ጉልህ ያደርገዋል ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌዴራሊዝም እና ገቨርናንስ መምህርና ተመራማሪ ተስፋዬ ጂማ(ዶ/ር)፤ የቀይ ባህር ቀጣና የዓለም ኃያላን መንግስታት ስትራቴጂካዊ የፍላጎት ማዕከል እየሆነ መምጣቱን ጠቁመዋል። የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ካለው ጂኦስትራቴጂክ ጠቀሜታ ባለፈ ለኢንዱስትሪ ዕድገት፣ ለቱሪዝም፣ ለባህል ልውውጥና ለግዙፍ የንግድ እንቅስቃሴዎች ምቹ መሆኑን አብራርተዋል። የቀጣናው ሀገራት ቀይ ባህርን በጋራ ማልማትና መጠቀም የሚያስችል ትብብር መፍጠር ከቻሉ ግዙፍ የኢኮኖሚ አቅም የመገንባት ዕድላቸውም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። ለዚህም በቀጣናው የሚከናወኑ የወደብና ሎጂስቲክ መሰረተ ልማት ግንባታዎች በትብብር መስራት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው፤ ለቀጣናው ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖ ፈጣሪነት አዎንታዊ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን ሰላማዊና በወንድማማችነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት በቀይ ባህር ያላት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ማድረግ ለጋራ ብልጽግና እውን መሆን ከፍተኛ ድርሻ አለው ነው ያሉት። በቀጣናው የጋራ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስር የሚፈጥር ተቋም መገንባት ወሳኝ መሆኑን አንስተው የቀይ ባህር አካባቢን ማልማትና መጠቀም ከሚያስገኘው ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ እና ጂኦ ፖለቲካዊ ጥቅሞች አኳያ ከተናጠል እንቅስቃሴ ይልቅ በጋራ መስራት የቀጣናው ሀገራት ቁልፍ አጀንዳ ሊሆን እንደሚገባም መክረዋል። በዩኒቨርሲቲው የሰላምና ደኅንነት ተመራማሪው ሙሉጌታ አየለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የሌሎች ሀገራትን ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅም የምታከብር መሆኗን ተናግረዋል። በጎረቤት ሀገራት መሪዎችና በሥርዓት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የሉዓላዊነት አቋም በተግባር ስታሳይ መቆየቷን ጠቁመውይህንኑ ታሪካዊ እውነት ከአፍሪካ ሕብረት ምስረታ ጀምሮ ያስመሰከረች ሀገር መሆኗን አስታውሰዋል።
አርሶ አደሮች ቡናን በጥራት አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ያላቸው ተነሳሽነት እያደገ መጥቷል - ሚኒስትር አዲሱ አረጋ
Dec 31, 2025 54
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በሁሉም ቡና አብቃይ ወረዳዎች በተደረገ የባለሙያ ድጋፍ አርሶ አደሮች ቡናን በጥራት አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ያላቸው ተነሳሽነት እየተሻሻለ መምጣቱን የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ገለጹ። በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ በቡና ልማት ላይ የተሳተፉ አርሶ አደር ማሳ የጎበኙት የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ እንዳሉት በተያዘው ዓመት 600ሺህ ቶን ቡና ለውጪ ገበያ ለማቅረብ ታቅዷል። ለውጭ ገበያ ከሚቀርበው የቡና ምርት ከ3 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት ግብ ተይዞ ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። በሲዳማ ክልሉ ቡና አምራች በሆኑ አካባቢዎች የቡና ጥራትና ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚ ለመሆን እየተሰራ ያለው ሥራ በዘርፉ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል። የቡና ዝርያን ለማሻሻል፣ የአመራረት ዘዴን ለማዘመን፣ ኩታ ገጠም የቡና ልማትን ለማስፋፋትና ምርታማነታቸው የተረጋገጠ የቡና ዝርያዎችን ለማልማት የተሰራው ሥራ ዕቅዱን ለማሳካት እንደሚያስችል ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያን ቡና በቻይና የማስተዋወቅ ሥራ እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ በተለይ ከባለ ልዩ ጣዕም ቡና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በቀጣይ በተለያዩ ሀገራት የማስተዋወቅ ሥራ ይሰራል ብለዋል። ዘንድሮ ለውጪ ገበያ ለማቅረብ የተያዘውን ዕቅድ ማሳካት የሚያስችሉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እንዳሉ ጠቁመው፣ በሁሉም ቡና አብቃይ ወረዳዎች በተደረገ የባለሙያ ድጋፍ አርሶ አደሮች ቡናን በጥራት አምርቶ ለማቅረብ ያላቸው ተነሳሽነት መሻሻሉን ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ ቡና እና አቮካዶ ለውጪ ገበያ እንደሚቀርብ ታሳቢ ተደርጎ እየሰተራ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን በመጠቀም የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው አዳዲስ የቡና ዝርያዎችን መጠቀምን ጨምሮ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በእርጅና ምክንያት ምርታማነቱ የቀነሰ የቡና ተክልን በአዲስ የመተካትና ባህር ዛፍን ነቅሎ በቡና የመተካት ሥራ እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። የክልሉ ቡና፣ ቅመማቅመምና ፍራፍሬ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ በክልሉ በተያዘው ዓመት ወደ ውጪ ከሚላከው 40ሺህ ቶን ቡና 17 በመቶ የሚሆነው ባለልዩ ጣዕም እንደሚሆንና ይህንንም በሂደት ወደ 20 በመቶ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አርሶ አደሮችም ባለልዩ ጣዕም ቡና አምርተው ለውጪ ገበያ በራሳቸው በቀጥታ መላክ እንዲችሉ ለ400 አርሶ አደሮች ፈቃድ በመስጠት ክትትልና ደጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም ተናግረዋል። በክልሉ ሸበዲኖ ወረዳ ባለልዩ ጣዕም ቡና አምርተው ለውጪ ገበያ ቀጥታ ለማቅረብ ፈቃድ ከተሰጣቸው አርሶ አደሮች መካከል ቦዳ ሳጉና እንዳሉት በሁለት ሄክታር መሬት ቡና እንዳለሙና ከሄክታር 30 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል። ያመረቱትን ምርት በቀጥታ ወደ ውጪ ለመላክ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመው ከክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ እና ከቡና፣ ቅመማቅመምና ፍራፍሬ ባለስልጣን ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው
Dec 31, 2025 26
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ገለጹ። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለአምስት ተከታታይ ቀናት የተካሄደው ሁለተኛው የብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ(ግሪን ሞቢሊቲ) አውደ ርዕይና ፎረም 2025 ተጠናቋል። በአውደ ርዕይና ፎረሙ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን፤ የዘንድሮው ዓውደ ርዕይ ዓላማውን ያሳካና ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተካሄዱ የውይይት መድረኮችም በርካታ አካላትን ያገናኙና ውጤታማ መረጃዎች የተለዋወጡባቸው መሆናቸውን ጠቁመዋል። በአውደ ርዕዩ ኢትዮጵያውያን በዘርፉ ላይ የላቁ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ሥራዎችን በማቅረብ ሻጮችና ሸማቾች የተገናኙበት ትልቅ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ ብሩህ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ሀገሪቱ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የጀመረቻቸውን ውጤታማ ሥራዎች አጠናክራ እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል። በአሁኑ ወቅት የአረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዓውደ ርዕዩ አዳዲስ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ መቅረባቸውንና ዘርፉ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም ያለውን ፋይዳ በተመለከተም የጋራ ግንዛቤ የተፈጠረበት እንደሆነ ገልጸዋል። ለአውደ ርዕዩ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ ተሳታፊዎች ምስጋና አቅርበው፤ በመጪው ዘመን በፈጠራው ዘርፍ የተሻሉ ሥራዎች እንደሚጠበቁም አመልክተዋል። ዓውደ ርዕዩ በቀጣይም ይበልጥ እንዲሳካ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ተጋላጭነት ለመውጣት የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭን ጨምሮ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማስፋፋት በኩል ውጤታማ የአረንጓዴ ልማት እርምጃዎችን እየወሰደች እንደምትገኝም በዚሁ ወቅት ተመልክቷል።
በከተማው ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እያገዘ ነው
Dec 31, 2025 26
ጎንደር፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የዜጎችን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመፍታት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው ተናገሩ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ መሬት መምሪያ ዘመናዊ የመሬት ይዞታ መረጃን በዲጂታል የመረጃ ስርዓት መምራት የሚያስችለውን የካዳስተር አሰራር በይፋ በማስመረቅ ዛሬ አስጀምሯል፡፡ በምረቃው የተገኙት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው እንደተናገሩት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ኢንሼቲቭ ከተሞች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የዲጂታል አገልግሎት እንዲሰጡ መሰረት የጣለ ነው። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ዜጎች ማናቸውንም የመንግስት አገልግሎቶች ፈጣንና ቀልጣፋ በሆነ መልኩ እንዲያገኙ አስቻይ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግ ልማትና እድገትን ለማፋጠን አዎንታዊ ሚና እንዳለውም ነው የተናገሩት፡፡ የመሬት ይዞታ መረጃ ስርዓቱ ዲጂታል መደረጉ በከተማዋ ህገ ወጥ ግንባታንና የመሬት ወረራን ለመቆጣጠር ብሎም በዘርፉ ይስተዋሉ የነበሩ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡ የካዳስተር ሥርዓት የከተማውን የመሬት ሀብት በአግባቡ ቆጥሮና ለይቶ በማደራጀት አልምቶ ለመጠቀም ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ መሬት መምሪያ ሃላፊ ትዛዙ በጽሃ ናቸው፡፡ የካዳስተር ስርዓት በተተገበረባቸው ከ2010 እስከ 2017 ባሉት ዓመታት ከ21ሺህ በላይ የመሬት ይዞታዎችን የመለየትና መረጃ የማሰባሰብ ሥራዎችን በቴክኖሎጂ ታግዞ ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመትም ከ15ሺህ በላይ ይዞታዎችን መረጃ ማሰባሰቡን ገልጸው፣ ሁሉንም ይዞታዎች ወደ መረጃ ቋት በማስገባት በአሁኑ ወቅት ይዞታቸው ለተረጋገጠላቸው ነዋሪዎች ዲጂታል ካርታ የመስጠት ሥራ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡ በዛሬው እለት ዲጂታል ካርታ ከተረከቡ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ሃና ማለደ በሰጡት አስተያየት ዲጂታል ካርታ ዜጎች አስተማማኝ የይዞታ ማረጋገጫ አንዲኖራቸው ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ዲጂታል ካርታ ከዚህ ቀደም በመሬት ይዞታ ይረጋገጥልኝ ጥያቄ ላይ ያጋጥሙ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን የሚያስቀርና ከእንግልት የሚታደግ በመሆኑ መደሰታቸውን የገለጹት ደግሞ አቶ አህመድ ለጋስ ናቸው።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የመዲናዋን የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት ለማላቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል
Dec 31, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የመዲናዋን የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማላቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬታማነት የማጠናቀቂያና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ማብሰሪያ መርሃግብር መካሄዱ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅትም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር፣ የዜጎችና ተቋማትን መተማመን ማጎልበት ቁልፍ ትልሞች መሆናቸውን አጽንኦት ሰጥተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የኢንዱስትሪ ምርታማነትን የሚያሳልጥ መሰረት ተጥሏል። የዲጂታል ዓለም በሰው ሰራሽ አስተውሎት የፈጠረው ከፍተኛ አቅም ለኢንዱስትሪ የምርት ጥራትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት መልካም አጋጣሚዎችን እየፈጠረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የዲጂታላይዜሽን ሥርዓትም ለመዲናዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ቁጥርና የምርታማነት አቅም በማላቅ ወሳኝ ሚና እየተወጣ መሆኑን አስረድተዋል። በአዲስ አበባ ከተማም ከ3 ሺህ 824 በላይ ኢንዱስትሪዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥርዓት የታገዘ ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ ምርት ለገበያ በመቅረብ እመርታዊ ለውጥ እያመጡ መሆኑን አስገንዝበዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ቁልፍ ትልሞችም የኢንዱስትሪ ምርታማነትን በማላቅ ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ግዙፍ የውድድር መድረክ እየሆነ በመጣው የዲጂታላይዜሽን ሥርዓት ውስጥ መሪ ተዋናይ ለመሆን ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ውጤት መጠቀም እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም በአዲስ አበባና በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማሩ አልሚዎች ምርታማነት ወሳኝ አቅም እንደሚፈጥር አንስተዋል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሁሉም ሆስፒታሎች የዲጂታል የጤና አገልግሎት እንዲሰጡ ይደረጋል
Dec 31, 2025 65
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሁሉም ሆስፒታሎች የጤና አገልግሎቶችን በዲጂታል መስጠት የሚችሉባቸው ግብዓቶች እየተሟሉ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የዜጎችን ጤናና ማህበራዊ ደህንነት ለማረጋገጥ ዓለም አቀፍና ሀገራዊ የጤና ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን ገቢራዊ አድርጋለች፡፡ በዚህም መከላከልን መሰረተ ባደረገው የጤና ፖሊሲዋ የእናቶችና ህፃናትን ሞት በመቀነስ በዘላቂ የልማት ግቦች የተቀመጡ ዕቅዶችን ቀድማ ማሳካት ችላለች፡፡ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሚኒስቴሩ የጤና ተቋማትን በግብዓት በማዘመን፣ በዲጂታል የታገዘ የጤና አገልግሎት በመስጠት ዲጂታል ቴክኖሎጂን በተሻለ የሚጠቀም ተቋም ነው፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለጤናው ዘርፍ መልካም ዕድል ይዞ መምጣቱን ገልጸው፤ በስትራቴጂው ማብቂያ አብዛኞቹ የጤና ተቋማት የመረጃ ስልታቸውን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ያስገባሉ ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በ2030 ሁሉም ሆስፒታሎች ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ አገልግሎት እንዲሰጡ አስፈላጊው የዲጂታል አገልግሎት ግብዓት እየተሟላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በማህበረሰብ አቀፍ የጤና ሥርዓት በቀበሌዎች ያለውን መረጃ በዲጂታል ሥርዓት ይዘው ሪፖርት የሚያደርጉበት አሰራር መኖሩንም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ይህንን አሰራር ሙሉ በሙሉ ገቢራዊ በማድረግ የዲጂታል አገልግሎት በጤናው ዘርፍ የላቀ አገልግሎት እንዲኖረው ይደረጋል ብለዋል፡፡ የጤና ተቋማትን ማዕከል ያደረጉ የመረጃ ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል ይገባሉ ያሉት ዶክተር ደረጀ፤ የጤና ባለሙያዎች ላይ ቁጥጥር የሚደረግበት አሰራር ገቢራዊ እንደሚደረግም ገልጸዋል፡፡ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ዜጎች ከቤታቸው ሆነው የጤና ምክርና አገልግሎት የሚያገኙበትን፣ ቀጠሮ የሚይዙበትን ቀላልና ቀልጣፋ እድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡ የታካሚዎች የህክምና መረጃ በቀላሉ ማግኘት የሚያስችል የዲጂታል ስርዓት ገቢራዊ እንደሚደረግ በመጥቀስ፤የዲጂታል መረጃ ስርዓቱን የሚያሳልጡ ግብዓቶች ወደ ሀገር ቤት እየገቡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ስፖርት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድል ቀንቶታል
Dec 31, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 12ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮጵያ መድንን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ናትናኤል ዳንኤል እና አዲስ ግደይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ረመዳን የሱፍ ለኢትዮጵያ መድን ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ ቢኒያም ካሳሁን በ73ኛው ደቂቃ ላይ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። በሊጉ ሶስተኛ ድሉን ያሳካው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ15 ነጥብ ደረጃውን ከ14ኛ ወደ 11ኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ13 ነጥብ ከነበረበት 13ኛ ደረጃ ወደ 14ኛ ዝቅ ብሏል። ዛሬ በተደረገ ሌላኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና መቻልን 1 ለ 0 አሸንፏል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የ12ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ13ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከታህሳስ 25 ቀን 2015 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ ቡና ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
Dec 31, 2025 37
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 12ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ቡና መቻልን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ናይጄሪያዊው ዲቫይን ዋቹኩዋ በ44ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ከሶስት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ኢትዮጵያ ቡና በ15 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 12ኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ አራተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቻል በ20 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል።
በአፍሪካ ዋንጫ ለበርካታ ጊዜ የተሰለፉ ተጫዋቾች
Dec 31, 2025 118
የአፍሪካ ዋንጫ የአፍሪካ እግር ኳስ ቁንጮ መድረክ ነው። ሀገራት በየሁለት ዓመቱ በአንድ መድረክ ተገናኝተው ዋንጫውን ለማንሳት ይፋለማሉ። ግቦች፣ ዋንጫዎች፣ ኮከብ ተጫዋቾች እና ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች የዜና አርዕስት ሆነው ጎልተው ይታያሉ። በአህጉራዊ መድረክ ብቃታቸው ሳይዋዥቅ ለረጅም ጊዜያት የተሰለፉ ተጫዋቾች የአፍሪካ እግር ኳስ ምልክቶች ናቸው። ካሜሮናዊው ተከላካይ ሪጎበርት ሶንግ 36 ጨዋታዎችን በማድረግ በርካታ ጨዋታዎች ላይ ከተሰለፉ ተጫዋቾች መካከል ይጠቀሳል። በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 12ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል ሶንግ በስምንት የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ በመሳተፍ አይበገሬነቱን አሳይቷል። በተጫዋችነት ዘመኑ ሁለት የአፍሪካ ዋንጫን አንስቷል። የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖም አገልግሏል። እንደ ሶንግ በተመሳሳይ 36 ጨዋታዎችን ያደረገው ጋናዊው አንድሬ አየው ነው። በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ስሙ ጎልቶ ከሚነሳው አብዲ ፔሌ ልጆች መካከል አንዱ የሆነው አንድሬ አየው በስምንት የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎን አድርጓል። ቡድኑ በሁለት አጋጣሚ የፍጻሜ ተፈላሚ እንዲሆን ማድረግ ችሏል። ጋና በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አለመሳተፏን ተከትሎ አየው የበርካታ ጊዜ የመሰለፍ ክብረ ወሰን የመስበር እድል አምልጦታል። ግብጻዊው አህመድ ሀሰን በስምንት የአፍሪካ ዋንጫ 32 ጨዋታዎችን በማድረግ ሌላኛው ተጫዋች ነው። ሀሰን አራት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን በማንሳት በስኬት ያሸበረቀ ታሪክ አለው። ማሊያዊው ሰይዱ ኬይታ፣ ካሜሮናዊው ጀረሚ ንጂታፕ እና ጋናዊው አሳሞሃ ጊያን በተመሳሳይ 31 ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫው ተሰልፈው ለሀገራቸው ተጫውተዋል። የኮትዲቯሩ ያያ ቱሬ፣ የናይጄሪያው ጆሴፍ ዮቦ፣ የካሜሮኑ ሳሙኤል ኤቶ እና የቱኒዚያው የሱፍ ምሳክኒ በተመሳሳይ 29 ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫው ተሰልፈዋል። ኮትዲቭዋርያኑ ማክስ-አለን ግራዴል እና ቡባካር ባሪ እንዲሁም ግብጻዊው ግብ ጠባቂ ኢሳም ኤል ሃዳሪ በተመሳሳይ 28 ጊዜ ጨዋታቸውን አድርገዋል። የኮትዲቭዋሮቹ ሲያካ ቲዬኔ እና ኮሎ ሃቢብ ቱሬ በተመሳሳይ በ27 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፈው ተጫውተዋል። የተጫዋቾቹ ለበርካታ ጊዜ መሰለፍ በአህጉራዊው መድረክ ለረጅም ጊዜ የመቆየት አቅም፣ አልሸነፍ ባይነት እና በጫና ውስጥ የማለፍ ብርታትን የሚያመላከት ነው።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 12ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል
Dec 31, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት በመጨረሻ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ መድን ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። የ2016 ዓ.ም የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሊጉ ካደረጋቸው 11 ጨዋታዎች መካከል ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ በሶስቱ ተሸንፏል። በስድስት ጨዋታዎች ላይ አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ 13 ግቦችን ሲያስቆጥር በተመሳሳይ 13 ጎሎችን አስተናግዷል። ንግድ ባንክ በ12 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ መድን በውድድር ዓመቱ 11 ጨዋታዎችን አከናውኖ በሶስቱ ድል ሲቀናው አራት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ አራት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። ዘጠኝ ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ጎሎች ተቆጥረውበታል። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ13 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ጨዋታ ትኩረትን ስቧል። በሌላኛው መርሃ ግብር መቻል ከኢትዮጵያ ቡና ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። መቻል እስከ አሁን በሊጉ 11 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን አራት ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። በስድስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በ11ዱ ጨዋታዎች ላይ 16 ጎሎችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ20 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ ካከናወናቸው 11 ጨዋታዎች መካከል ሶስት ጊዜ ድል ሲቀናው በአምስቱ ተሸንፏል። ሶስት ጊዜ ነጥብ ጥሏል። ዘጠኝ ግቦችን ሲያስቆጥር 11 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ኢትዮጵያ ቡና በ12 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው መቻል ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ኢትዮጵያ ቡና ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ሶስት ነጥብ ለማግኘት የሚያደርጉት ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የተከናወኑ የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ ሥራዎች ምርታማነትን አሳድገዋል
Dec 31, 2025 65
አዲስ አበባ፣ታኅሣስ 22/2018 (ኢዜአ)፡-ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ ሥራዎች ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻላቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ገልጿል። የቢሮው ምክትልና የተፈጥሮ ሐብት ዘርፍ ኃላፊ አብዱልከሪም ሙሳ እንዳሉት፤የዘንድሮው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ የፊታችን ጥር ወር ይጀመራል። በሁሉም ወረዳዎች በሚከናወነው ሥራም በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ አስታውቀዋል። በዚህም መሠረት ከ57 ሺህ ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ለማከናወን መታቀዱን ገልፀዋል። ባለፈው ዓመት በ52 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ ሥራ መከናወኑንም አውስተዋል። ቀደም ባሉት ዓመታት የተከናወኑ የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ ሥራዎች በርካታ ጥቅሞች ማስገኘታቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። ከእነዚህ ጥቅሞች መካከል የምርትና ምርታማነት መጨመር፣ የአፈር መሸርሸር መቀነስ፣ የምንጮች መጎልበትና የመስኖ ተጠቃሚነት ማደግ የሚሉትን ለአብነት ጠቅሰዋል። የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ ሥራ የሚያስገኘውን ዘርፈ-ብዙ ተጠቃሚነት በመገንዘብ በጥር ወር በሚጀመረው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ሕብረተሰቡ ተሳትፎውን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።
የዘላቂ ልማት ጥበቃ ፕሮጀክት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አስችሏል
Dec 30, 2025 135
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ሲተገበር የቆየው ግብርና ላይ የተመሰረተ የዘላቂ ልማት ጥበቃ ፕሮጀክት የአፈር ለምነትን በመጨመር ረገድ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን ግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በኢትዮጵያ እኤአ 2022-2025 ሲተገበር የቆየው ግብርና ላይ የተመሰረተ የዘላቂ ልማት ጥበቃ ፕሮጀክት(SCASI) አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል። ፕሮጀክቱ በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በሚገኙ ስምንት ወረዳዎች ላይ ሲተገበር መቆየቱ ተጠቁሟል፡፡ በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብትና የአፈር ለምነት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሊሬ አብዩ እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችን፣ የሰብል ማፈራረቅ ዘዴንና የአርሶ አደሩን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ይህም በተተገበረባቸው አካባቢዎች የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥና ድህነትን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመዋል። የዓለም የበቆሎና የስንዴ ምርምር ማዕከል የኢትዮጵያ አስተባባሪ ብርሃን አብዱልቃድር በበኩላቸው፤ ማዕከሉ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉና በአጭር ጊዜ የሚደርሱ የሰብል ዝርያዎችን በማውጣትና በማስፋፋት የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በሜካናይዜሽንና በምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ የተሰሩ ሥራዎች የአርሶ አደሩ ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በተለይ የስንዴ እና የበቆሎ ዝርያን በማሻሻል ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ እንደ የአካባቢ ስነ-ምህዳር የሚውሉ ዝርያዎችን እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የግብርና ኤክስቴንሽን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ቀኛዝማች መስፍን ፤ፕሮጀክቱ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ ያመጣው ለውጥ በተግባር መረጋገጡን ገልጸዋል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሰብል ልማት ጥበቃና ቴክኖሎጂ ማስፋፊያ ዳይሬክተር ፍቅሩ አቡን በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ በክልሉ ሁለት ወረዳዎች መተግበሩን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ የተገኘውን መልካም ተሞክሮ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማስፋት በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ
Dec 30, 2025 162
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዷል። የአዋጁን አስፈላጊነትም የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት እንዲሁም የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች በጋራ ያዘጋጁት ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቧል። በምክር ቤቱ የሁለቱን ቋሚ ኮሚቲ የውሳኔ ሃሳብ ሪፖርትም የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፈቲያ አህመድ አቅርበዋል፡፡ በሪፖርቱም ረቂቅ አዋጁ የሥርዓተ ምኅዳር ደኅንነትና ዘላቂነትን በማረጋገጥ ጥቅምና የተፈጥሮ አያያዝን ለማሻሻል ወሳኝ መሆኑን በሪፖርታቸው አመላክተዋል። በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ዋጋ ላይ የተፈጠረው ሳይንሳዊ ግንዛቤ ማደግ ለአዋጁ መውጣት መነሻ ምክንያት መሆኑንም አስረድተዋል። የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎቶች ለኢኮኖሚ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ በፖሊሲዎችና በውሳኔ አሰጣጥ ላይ እየተንጸባረቀ የሚገኝ መሆኑም ተገልጿል። በዚህም የሥርዓተ ምኅዳርን በዘላቂነት ለማስተዳደር የሚያስችል የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ የሕግ ማዕቀፍና የአሰራር ስርዓቶችን መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ በረቂቅ አዋጁ የውሳኔ ሀሳብ ገልጸዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም፤ በረቂቅ አዋጁ ላይ ቢሻሻሉና ቢካተቱ ያሏቸውን ምክረ ሃሳቦች በጥያቄና አስተያየት አቅርበዋል። በቀጣይም የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ የትግበራ አፈፃጸም ውጤታማነትን ለማስጠበቅ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በመጨረሻም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ስብሰባው የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን በመመርመር በአዋጅ ቁጥር 1401/2018 ዓ.ም በአንድ ድምፅ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡
በብሔረሰብ አስተዳደሩ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ሰፊ የውሃ አማራጮችና የልማት እድሎች አግኝተናል--ወጣቶች
Dec 30, 2025 104
ሰቆጣ፤ ታህሳስ 21/2018 (ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የውሃ አማራጮች በመስፋታቸው በመስኖ ልማት በመሰማራት ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን የሰቆጣ ከተማ ወጣቶች ገለፁ። የሰቆጣ ከተማ የ2018 የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ በ04 ቀበሌ ቦሹ ተፋሰስ ላይ ተጀምሯል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ የከርሰ ምድርና ገፀ ምድር የውሃ አማራጮችን በማሳደግ ከ700 በላይ ወጣቶች በንብ ማነብ፣ በከብት ማድለብና በአትክልት ልማት ስራ እንዲሰማሩ ማስቻሉም ተመልክቷል። በወቅቱም ወጣቶቹ፤ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የውሃ አማራጮች በመስፋቱ በመስኖ ልማት ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። በከተማው የ04 ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ወጣት ፋንታው ጌታወይ ለኢዜአ እንደገለፀው በአካባቢያቸው የሚገኘውን ቦሹ ተፋሰስ ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ መልሶ እንዲያገግም አድርገዋል። በእርከን የታገዘው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራው በተፋሰሱ ስር በሚገኙ አካባቢዎች የውሃ ማመንጨት አቅም በመጨመሩ ወጣቶች በመስኖ ልማት እንዲሰማሩ ማስቻሉን ገልጿል። "እኔ ከአሁን ቀደም ምንም ስራ አልነበረኝም" ያለው ወጣት ፋንታው አሁን ላይ ያለሙት ተፋሰሶች የውሃ አማራጮችን በማስፋታቸው በአትክልት ልማት ስራ ላይ ለመሰማራት መቻላቸውን ገልጿል። ሌላው የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት አወጣ ቸኮለ በበኩሉ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ ሽንኩርት፣ ቲማቲምና ድንች እያመረተ መሆኑን ተናግሯል። ያመረተውን ምርትም ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነቱን በማሳደግ ሃብት እያፈራ መሆኑን ገልጿል። በየዓመቱ የሚሰሩ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች በአግባቡ ከተጠበቁ ውጤት እንዳለው በቦሹ ተፋሰስ አረጋግጠናል ያለው ደግሞ ወጣት ፋንታው ፀሃዩ ነው። እያገኘን ያለነውን ጥቅም ዘላቂነት ለማረጋገጥም በዘንድሮው በጋ በሚካሄደው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ግንባር ቀደም ተዋናይ ለመሆን ስራውን መጀመራቸውን አስረድቷል። የሰቆጣ ከተማ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሚዛን ጌታወይ በከተማው ዙሪያ በሚገኙ ገጠር ቀበሌዎች የለሙ ተፋሰሶች ለወጣቱ የገቢ ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል። የለሙ ተፋሰሶች የአፈር ለምነትን በመጨመር የአርሶ አደሩ ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻላቸውን የገለጹት ደግሞ የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ናቸው። በተጨማሪም የከርሰ ምድርና ገፀ ምድር የውሃ አማራጮችን በማሳደግ ከ700 በላይ ወጣቶች በንብ ማነብ፣ በከብት ማድለብና በአትክልት ልማት ላይ እንዲሰማሩ ማስቻሉን አስረድተዋል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ በተያዘው ዓመት በ366 ተፋሰሶች ላይ የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ማካሄድ መጀመሩን አስረድተዋል። እየተሰሩ ያሉ ተፋሰሶችን ዘላቂነት ለማረጋገጥም የተፋሰሶች ህብረት ስራ ማህበራት በማቋቋም የተጠናከረ ጥበቃና እንክብካቤ እንዲደረግ መሰራቱንም አብራርተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፤ የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ዋና የትኩረት አጀንዳ
Dec 26, 2025 324
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ነው። መሪ ሀሳቡን ያረቀቀው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የዘንድሮው መሪ ቃል ከአጀንዳ 2063 ጋር የተቆራኘ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። ሁሉም አፍሪካዊ ንጹህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በቂ ውሃ ለመጠጥ፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለሌሎች ፍላጎቶቹ እንዲያገኝ የማድረግ ራዕይን ለማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል። ህብረቱ የውሃ ደህንነት እንደ አህጉር የተያዙ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማዕቀፎቹ አስቀምጧል። ውሃ እና ንጽህና የኢኮኖሚ እድሎችን በማስፋት፣ የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ፣ የስደቶችና ተፈናቃዮችን ጫና ለማቃለል እንዲሁም ለሰላምና ደህንነት መስፈን አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተመላክቷል። የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ህብረቱ ውሃ እና ንጽህና ለጤና፣ ለኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥና ዘላቂ የአካባቢ ምህዳር ለመፍጠር መሰረት መሆኑን የበለጠ እውቅና እንደተሰጠው አመልክቷል። ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይገበር የውሃ ደህንነትን የማረጋገጥ አላማ ካለው የአፍሪካ የውሃ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው። የዘንድሮው መሪ ቃል የአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጥረቶችን ያስተሳሰረ ድልድይ ሆኗል። በዘላቂ ልማት ግቦች ውስጥ ያለው ግብ ስድስት ከውሃ እና ንጽህና ጋር የተያያዘ ነው። ይህ ግብ እ.አ.አ በ2030 ለሁሌም ዜጋ ደህንነቱ የተረጋገጠ ውሃ አቅርቦትና የንጽህና አጠባበቅን ተደራሽ የማድረግ አላማ አለው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት በፍጥነት መስፋፋትና ውሃ በአግባቡ አለመጠቀም የውሃ ደህንነት እና ዘላቂ አቅርቦት ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። የንጽህና አጠባበቅ የአፍሪካ አንዱ ፈተና ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች መሰረታዊ የሚባል የንጽህና መጠበቂያ መሰረተ ልማቶችን አያገኙም። ይህም እንደ ኮሌራ ላሉ የውሃ ወለድ በሽታዎች መስፋፋት ምክንያት ሆኗል። የተቀናጀ የውሃ አስተዳደር ስርዓት፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ ለዘላቂ መሰረተ ልማት የሚፈሰወን መዋዕለ ንዋይን ማሳደግ፣ ውሃ በድጋሚ አጣርቶ መጠቀም፣ የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ፣ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር እና ለውሃ ደህንነት ትኩረት የሚሰጡ ፖሊሲዎችና ማዕቀፎችን በውጤታማነት መተግበር ያሉትን እድሎች በዘላቂነት ለመፍታትና ፈተናዎችን ለመቅረፍ ያስችላል። ደህንነቱ የተረጋገጠ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ላይ ያለፈውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የቆሸሸ ውሃ በአግባቡ ማከም፣ የንጽህና አጠባበቅ ማስፋትና የግንዛቤ ፈጠራ ስራን በስፋት ማከናወን፣ ማህበረሰብ መር የንጽህና አጠባበቅ ኢኒሼቲቮችን ትግበራ ማስፋት፣ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎችና ሀገር በቀል አቅምን መገንባት ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓትን መፍጠር ያስችላል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና ጤናማ ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸውን ቁልፍ ሚና የሚያሳይ ነው። የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግ መሰረታዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰብ ደህንነትና የተሻለ የኑሮ ዘይቤ፣ ለአካባቢ ጥበቃና ለአፍሪካ ብልጽግና መረጋገጥ ስትራቴካዊ አቅም ናቸው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በሚካሄድበት ወቅት በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም እና 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኞች ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የአፍሪካ ጣሊያን ስብሰባን ለማዘጋጀት ብሄራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 319
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጸንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው-ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
Dec 23, 2025 281
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እና ለረጅም ጊዜ ፀንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኃላፊ አምባሳደር ኮንስታንሲያ አዴሊና ጋስፓራስ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት (ዋይት ሃውስ) በተካሄደ ስነ ስርዓት የአምባሳደር ኮንስታንሲያን ሹመት በይፋ ተቀብለዋል። አምባሳደሯ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ቢሮ ስራቸውን በይፋ ጀምረዋል። ዶናልድ ትራምፕ የአምባሳደር ኮንስታንሲያ የልዑኩ መሪ ሆኖ መመረጥ በጋራ የኢኮኖሚ እድሎች፣ በሉዓላዊ አመራር ሰጪነት እንዲሁም በሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጽኑ አጋርነት የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በአፍሪካ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋትን ማረጋገጥን ዋና ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የአጋርነት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኝ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 332
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 170
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 249
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 474
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 641
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 877
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3228
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 3153
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 4059
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2727
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1742
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7555
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6047
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ወንድማማቾች በአፍሪካ ዋንጫ
Dec 29, 2025 181
የአፍሪካ ዋንጫ መልከ ብዙ ውድድር ነው። የሀገራት ተቀናቃኝነት፣ ታሪካዊ ገድሎች፣ አይረሴ የተጫዋቾች የግል ብቃት፣ ጨዋታ ወሳኝ ግቦች እና ዋንጫን ከፍ አድርጎ የማንሳት የኩራት እና የሀገር ፍቅር ስሜት መገለጫዎቹ ናቸው። ከሚቆጠሩ ግቦች እና ዋንጫዎች ባለፈ ቤተሰባዊ ገጽታ ያለው ነው። የአፍሪካ ዋንጫ በርካታ ወንድማማች ተጫዋቾች በአንድ ሀገር ማልያ ሲጫወቱ የተመለከትንባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው። በአህጉራዊው መድረክ የ68 ዓመታት ጉዞ አብረው የተጫወቱ ወንድማቾች በዚሁ ጽሁፍ እንመለከታለን። 1. ኢታሎ እና ሉቺያኖ ቫሳሎ (ኢትዮጵያ) ኢታሎ ቫሳሎ እና ሉቺያኖ ቫሳሎ በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጫወቱ ወንድማማቾች መሆናቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1962 ባዘጋጀችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የቫሳሎ ወንድማማቾች አንድ ላይ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጫውተዋል። ሉቺያኖ በውድድሩ ላይ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ከግብጹ ባደዊ አብድል ፈታህ ጋር በጋራ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ አጠናቋል። ሉቺያኖ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠ ሲሆን ይህም በውድድሩ ታሪክ የኮከብ ተጫዋችነትን ሽልማት ያገኘ የመጀመሪያው ተጫዋች እንዲሆን አስችሎታል። ኢትዮጵያ በወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳቷ የሚታወስ ነው። 2. ሆሳም እና ኢብራሂም ሀሰን (ግብጽ) ሆሳም ሀሰን እና ኢብራሂም ሀሰን በአፍሪካ ዋንጫው ስኬታማ የሚባሉ ወንድማማች ተጫዋቾች ናቸው። እ.አ.አ በ1986 ግብጽ ያስተናገደችውን 15ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና እ.አ.አ በ1998 በቡርኪናፋሶ የተካሄደውን 21ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ግብጽ ስታነሳ የቡድኑ አባላት ነበሩ። ወንድማማቾቹ የአፍሪካ ዋንጫን ሁለት ጊዜ በማንሳት ባለ ክብረ ወሰን ናቸው። የ59 ዓመቱ ሆሳም ሀሰን በአሁኑ ሰዓት የግብጽ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነው። በተጫዋችነቱ በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የምንጊዜውም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። 3. አልበርት ባዋንጋ እና ሮበርት ካዛዲ (ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ) ሁለቱ ወንድማማቾች ግብጽ እ.አ.አ በ1974 ባዘጋጀችው ዘጠነኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። በወቅቱ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ዛምቢያን በማሸነፍ ዋንጫውን ስታነሳ የታሪካዊው ድል አካል ነበሩ። 4. አንድሬ ካና ቢይክ እና ፍራንስዋ ኦማም ቢይክ (ካሜሮን) ሁለቱ ወንድማማቾች በሶስት የአፍሪካ ውድድሮች ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። ተጨዋቾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ በአህጉራዊ መድረክ በጋራ የመሰለፍ እድል ያገኙት እ.አ.አ በ1988 በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው 16ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። እ.አ.አ በ1990 በአልጄሪያ በተካሄደው 17ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ሴኔጋል እ.አ.አ በ1992 ባዘጋጀችው 18ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። ጣልያን እ.አ.አ በ1990 ባዘጋጀችው 14ኛው የዓለም ዋንጫ ከወንድማማቾቹ ታናሹ ፍራንስዋ ኦማም ቢይክ ካሜሮን አርጀንቲናን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ባስቆጠራት ጎል ሁሌም በሀገሬው ሰዎች ሲወሳ ይኖራል። 5. አንድሬ አየው እና ጆርዳን አየው (ጋና) ጋናውያኑ ወንድማሞች የአፍሪካ ዋንጫ ሲነሳ ሁሌም የሚታወሱ ተጫዋቾች ናቸው። በስድስት የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ አብረው ተሰልፈዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው የሰለፉት ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን እ.አ.አ በ2012 ባዘጋጁት 28ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። የአየው ወንድማማቾች እ.አ.አ በ2015 ኢኳቶሪያል ጊኒ ባዘጋጀችው 30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማንሳት ተቃርበው የነበሩ ቢሆንም በፍጻሜው በኮትዲቭዋር በመለያ ምት ተሸንፈው ህልማቸው ሳይሳካ ቀርቷል። የታዋቂው አፍሪካዊ ተጫዋች አብዲ ፔሌ ልጆች የሆኑት አንድሬ እና ጆርዳን አየው እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለመጨረሻ ጊዜ በጋራ ተሰልፈዋል። ጋና እ.አ.አ በ2008 ባዘጋጀችው 26ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ጋናዊው አጥቂ አሳሞሃ ጊያን እና ታናሽ ወንድሙ ባፎር አንድ ላይ ተጫውተዋል። በተጨማሪም በዛው ውድድር ላይ ጋናውያኑ ወንድማማቾች ሪቻርድ ኪንግስተን እና ላሪያ ጊንግስተን አብረው የመጫወት እድል አግኝተዋል። 6. ኮሎ ቱሬ እና ያያ ቱሬ (ኮትዲቭዋር) በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ስማቸው በግንባር ቀደምትነት ከሚነሱ ተጫዋቾች መካከል ኮሎ ቱሬ እና ያያ ቱሬ ይጠቀሳሉ። ወንድማማቾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው የተሰለፉት እ.አ.አ በ2006 በግብጽ አስተናጋጅነት በተካሄደው 25ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። በወቅቱ ኮትዲቭዋር ለፍጻሜ ደርሳ በግብጽ ተሸንፋለች። ኢኳቶሪያል ጊኒ እ.አ.አ በ2015 ባዘጋጀችው 30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኮትዲቭዋር ጋናን በማሸነፍ ዋንጫውን ለሁለተኛ ጊዜ ስታነሳ በጋራ የድሉ ተቋዳሽ ሆነዋል። የቱሬ ወንድማማቾች ለስድስት ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫው አብረው ተጫውተዋል። 7. የሞሪታኒያ እና ዛምቢያ ወንድማማች ተጫዋቾች እ.አ.አ በ2023 ኮትዲቭዋር ባስተናገደችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሪታኒያ ብሄራዊ ቡድን ስብስብ ከሁለት ቤተሰብ በተመሳሳይ ሁለት ወንድማማቾች መሳተፋቸው የተለየ ትኩረት ስቧል። ኑህ መሐመድ አብድ እና ታናሹ ሲዲ መሐመድ አህመድ አብድ በተከላካይ እና አማካይ መስመር ላይ ተሰልፈው ተጫውተዋል። ላሚን ባ እና ኤል ሃጂ ባ ለሞሪታኒያ ብሄራዊ ቡድን በመሰለፍ መጫወት ችለዋል። ዛምቢያዊያኑ ክርስቶፈር እና ፍሊክስ ካቶንጎ እ.አ.አ በ2012 ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን በጣምራ ባዘጋጁት 28ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛምቢያ ኮትዲቭዋር በማሸነፍ የአፍሪካ ዋንጫን ስታነሳ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2013 ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይም በጋራ ተሰልፈው ተጫውተዋል። ዛምቢያውያኑ ወንድማማቾች ኬኔት እና ሞርዶን ማሊቶሊ እ.አ.አ በ1994 በቱኒዚያ በተካሄደው 19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ1996 ባዘጋጀችው 20ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አንድ ላይ ተሰልፈዋል። አለን ትራኦሬ እና ኢብራሂማ ትራኦሬ (ቡርኪናፋሶ) በ30ኛው እና 31ኛው የአፍሪካ ፣ ሳምቡ ያታባሬ እና ሙስጠፋ ያታባሬ (ማሊ) በተመሳሳይ በ30ኛው እና 31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ፒተር ንዶልቩ እና አዳም ንዶልቩ (ዚምባቡዌ) በ24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ሳሉ፣ ባቺሩ እና ታጁ (ቶጎ) በ22ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ቾሞጎ ኦማር እና ሴዲያት ኦማር (ቤኒን) በ24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ መሐመድ እና ሙሳ ካሎን (ሴራሊዮን) በ20ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ሳሚር ሳሊሚና አዴል ሳሊሚ (ቱኒዚያ) በ19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አብረው የተሰለፉ ተጫዋቾች ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫ ከተሰለፉ ወንድማማቾች መካከል ስድስቱ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳታቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታውቋል።
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር ተሻጋሪ ወዳጅነት
Dec 16, 2025 596
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።