አርእስተ ዜና
ባንኩ በትግራይ ክልል ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Jan 16, 2025 37
መቀሌ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትግራይ ክልል ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ግንባር ቀደም አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞችን ቀን ምክንያት በማድረግ ዛሬ በመቀሌ ከተማ ከባለሀብቶች ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል።   በምክክር መድረኩ የተገኙት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ በክልሉ በነበረው ችግር ተቀዛቅዞ የቆየው የኢኮኖሚ እንቀስቃሴ እንዲነቃቃ ባንኩ ያደረገውን አስተዋጽኦ አድንቀዋል። የንግዱ ማህበረሰብ ያለውን የፋይናንስ ፍላጎት እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አጥንቶ የሚሰጠውን በጎ ምላሽና የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይብልጥ እንደሚያጠናክር እምነታቸው መሆኑንም ገልጸዋል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የፋይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ሀላፊ ምህረት በየነ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የክልሉ ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ የንግድ ባንክ ድርሻ የጎላ ነው ብለዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ነጋ ገብረ ስላሴ የተባሉ ባለሀብት በሰጡት አስተያየት፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን አገልግሎት እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።   ሌላው ባለሃብት አቶ መሐሪ ፍስሀ፤ ንግድ ባንኩ ራሱን ለማዘመን እየሰራቸው ያሉት ስራዎች ይበልጥ ሊያጠናክር ይገባል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመቀሌ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ልሳነወረቅ በበኩላቸው ባንኩ የሚተማመንባቸው ደንበኞች በክልሉ መኖራቸውን ገልፀዋል። ንግድ ባንኩ የብድር አገልግሎትን ለማሻሻልና አገልግሎቱን ለማዘመን በመስራት ላይ መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይም አገልግሎቱን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመቀሌ ዛሬ ባዘጋጀው የደንበኞች አገልግሎት መድረክ በተለያዩ የልማትና የንግድ ስራዎች የተሰማሩ ባለሀብቶች ተሳትፈዋል።
ርዕደ መሬት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ሁሉን አቀፍ የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jan 16, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ ርዕደ መሬት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ሁሉን አቀፍ የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የርዕደ መሬት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዝግጁነታችንና የምላሽ ሁኔታችን ባለን ቴክኖሎጂ፣ ሳይንሳዊ ምርምር፣ ትንተናና የትንበያ አቅም የሚወሰን ነው ብለዋል።   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ የስፔስ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት ዛሬ ዛሬ በተደረገው ጉብኝት በርዕደ መሬት ነክ ሳይንሳዊ ምርምር አበረታች ስራዎች ለመመልከት መቻሉን ተናግረዋል። ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በርዕደ መሬት ክስተት ዙሪያ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ተጠናከረ ተግባር መገባቱን ጠቁመዋል።   አደጋው በተከሰተባቸው አካባቢዎች የመሠረተ-ልማት፣ የጊዜያዊ መጠለያ፣ የሰብአዊ ድጋፍ፣ የሳይንሳዊ ትንተና እና ትንበያ ቡድኖችን በማደራጀት በዕቅድ ላይ የተመሰረተ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥት የአጭርና የረጅም ጊዜ ሀገራዊ ዝግጁነትን ለማጎልበት የጥናትና ምርምር ተቋማት ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂና ብቁ የሰው ኃይል ጠንካራ ቁመና እንዲፈጥሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚጠጉ የወተት ላሞች በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ ተዳቅለዋል - የክልሉ ግብርና ቢሮ
Jan 16, 2025 37
አዳማ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚጠጉ የወተት ላሞች በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ መዳቀላቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የእንስሳት ማሻሻያና ልማት ዳይሬክተር አቶ ደምሴ ኩምሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የወተት ላሞች የዝሪያ ማሻሻልና የእንስሳት ሀብት ልማት ኢንሼቲቭ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።   የወተት ሀብት ልማትን በመጨመር የወተትና ወተት ተዋፅዖ ወጤቶች በበቂ ደረጃ ተደራሽ በማድረግ ስርዓተ ምግብን ለማሻሻል የተጀመረውን የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በእስካሁኑ ሂደት የሀገረ ሰብ ላሞች በአማካይ በቀን 1 ነጥብ 5 ሊትር ወተት እንደሚገኝ የጠቀሱት ዳይሬክተሩ በተሻሻሉ የወተት ላሞች የወተት ምርቱን በቀን ወደ 12 ነጥብ 5 ለማሳደግ መታቀዱን ገልጸዋል። በክልሉ ባለፈው ዓመት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የወተት ላሞች በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ የተዳቀሉ ሲሆን በዚህ ዓመት 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን የወተት ላሞችን በመደበኛና በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ የማዳቀል ስራ እየተካነወነ ነው ብለዋል።   በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት በሁሉም የክልሉ ዞኖች በዘመቻ መልክ በተሰራው ስራ በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ የወተት ላሞች ማዳቀል መቻሉን ጠቅሰዋል። በዚህም የወተት ምርት ልማትና እድገት እየጨመረ መሆኑን ጠቅሰው በክልሉ በዘርፉ የተቀመጠውን የሌማት ትሩፋት ለማሳካት የተሻለ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የወተት መንደሮችን የማደራጀት ስራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቅሰው በወተት ላሞች ዝርያ ማሻሻያ የተቀመጠውን ግብ ማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ የሆኑ የሀዋሳ ዙሪያ አርሶ አደሮች
Jan 16, 2025 39
ሀዋሳ ጥር 8/2017 (ኢዜአ):- በአካባቢያቸው የተገነቡ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች በልማቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ አርሶ አደሮች ገለጹ። በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የጋሎ አርጊሳ ቀበሌው አርሶ አደር ታምራት ሄርቃሎና አርሶ አደር ሽንኩራ ሹናለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ ተመርቆ ወደ ሥራ የገባውን የኤጀርሳ መስኖ ፕሮጀክት ተጠቅመው 1 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት የተለያዩ የአትክልትፋ ፍራፍሬ ሰብሎችን በመስኖ እያለሙ ነው።     በመስኖ ልማት የሥራ ዕድል የተፈጠረለት ወጣት ታደሰ ህዝቄል በበኩሉ፤ ሰርቶ ያገኘውን ገንዘብ በመቆጠብ ላሞችን መግዛቱን ጠቁሞ በቀጣይ በመስኖ ልማት የመሰማራት ዕቅድ እንዳለው ገልጿል። የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሃይሉ ሁሪሳ በበኩላቸው በወረዳው ያለውን የውሃ አቅም በመጠቀም ከ5 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ በማልማት 12 ሺህ 500 አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በወረዳው ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ሦስት ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ዘንድሮ ወደስራ መግባታቸውን የገለጹት ደግሞ የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ገጠር ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ አሰፋ ፎና ናቸው። በሦስቱም የመስኖ ፕሮጀክቶች የመስኖ ልማት ሥራው እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው በልማቱ የአርሶ አደሩን ገቢ ከማሳደግ ባለፈ ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የልደታ ክፍለ ከተማን የአስተዳደር ሕንፃ መርቀው ከፈቱ
Jan 16, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በልደታ ክፍለ ከተማ የተገነባውን ባለ 13 ወለል የአስተዳደር ሕንጻ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል። ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ዛሬ ባለ 13 ወለል የልደታ ክፍለከተማ አስተዳደር ሕንፃ ግንባታን አጠናቅቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ሲሉ አስፍረዋል።   ዘመኑን የሚመጥን የስራ አካባቢ ለመፍጠር በተለያዩ አካባቢዎች ተበታትነው ሲሰጡ የነበሩትን አገልግሎቶች ወደ አንድ ማእከል በማሰባሰብ አገልግሎት የሚያሳልጥ ፣ ለአካል ጉዳተኞችም ምቹ፣ የአገልጋይና የተገልጋይ እንግልት የሚቀንስ፣ ስማርት ሲቲን የመፍጠር ግባችንን ለማሳካት የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ተካተውበት የተገነባ ነው ብለዋል። በውስጡ 120 ቢሮዎችን ጨምሮ እያንዳንዳቸው 1ሺ 500 እና 500 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ሁለት የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ በቂ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ ጂምናዚየም፣ የሕፃናት ማቆያና መጫወቻ ቦታ እና መሰል መገልገያዎች ተሟልተዉለታል ሲሉም ገልጸዋል። በተጨማሪ ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት በጥራት ገንብተን ያጠናቀቅነው ይህ ህንፃ ወጪን በመቆጠብ ከዚህ በፊት ለቢሮ ኪራይ የምናውለውን ሀብት በማስቀረት ለልማት እንድናውል ያስችለናል ብለዋል።
የሚታይ
ባንኩ በትግራይ ክልል ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Jan 16, 2025 37
መቀሌ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትግራይ ክልል ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ግንባር ቀደም አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞችን ቀን ምክንያት በማድረግ ዛሬ በመቀሌ ከተማ ከባለሀብቶች ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል።   በምክክር መድረኩ የተገኙት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ በክልሉ በነበረው ችግር ተቀዛቅዞ የቆየው የኢኮኖሚ እንቀስቃሴ እንዲነቃቃ ባንኩ ያደረገውን አስተዋጽኦ አድንቀዋል። የንግዱ ማህበረሰብ ያለውን የፋይናንስ ፍላጎት እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አጥንቶ የሚሰጠውን በጎ ምላሽና የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይብልጥ እንደሚያጠናክር እምነታቸው መሆኑንም ገልጸዋል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የፋይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ሀላፊ ምህረት በየነ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የክልሉ ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ የንግድ ባንክ ድርሻ የጎላ ነው ብለዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ነጋ ገብረ ስላሴ የተባሉ ባለሀብት በሰጡት አስተያየት፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን አገልግሎት እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።   ሌላው ባለሃብት አቶ መሐሪ ፍስሀ፤ ንግድ ባንኩ ራሱን ለማዘመን እየሰራቸው ያሉት ስራዎች ይበልጥ ሊያጠናክር ይገባል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመቀሌ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ልሳነወረቅ በበኩላቸው ባንኩ የሚተማመንባቸው ደንበኞች በክልሉ መኖራቸውን ገልፀዋል። ንግድ ባንኩ የብድር አገልግሎትን ለማሻሻልና አገልግሎቱን ለማዘመን በመስራት ላይ መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይም አገልግሎቱን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመቀሌ ዛሬ ባዘጋጀው የደንበኞች አገልግሎት መድረክ በተለያዩ የልማትና የንግድ ስራዎች የተሰማሩ ባለሀብቶች ተሳትፈዋል።
ርዕደ መሬት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ሁሉን አቀፍ የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jan 16, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ ርዕደ መሬት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ሁሉን አቀፍ የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የርዕደ መሬት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዝግጁነታችንና የምላሽ ሁኔታችን ባለን ቴክኖሎጂ፣ ሳይንሳዊ ምርምር፣ ትንተናና የትንበያ አቅም የሚወሰን ነው ብለዋል።   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ የስፔስ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት ዛሬ ዛሬ በተደረገው ጉብኝት በርዕደ መሬት ነክ ሳይንሳዊ ምርምር አበረታች ስራዎች ለመመልከት መቻሉን ተናግረዋል። ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በርዕደ መሬት ክስተት ዙሪያ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ተጠናከረ ተግባር መገባቱን ጠቁመዋል።   አደጋው በተከሰተባቸው አካባቢዎች የመሠረተ-ልማት፣ የጊዜያዊ መጠለያ፣ የሰብአዊ ድጋፍ፣ የሳይንሳዊ ትንተና እና ትንበያ ቡድኖችን በማደራጀት በዕቅድ ላይ የተመሰረተ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥት የአጭርና የረጅም ጊዜ ሀገራዊ ዝግጁነትን ለማጎልበት የጥናትና ምርምር ተቋማት ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂና ብቁ የሰው ኃይል ጠንካራ ቁመና እንዲፈጥሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የልደታ ክፍለ ከተማን የአስተዳደር ሕንፃ መርቀው ከፈቱ
Jan 16, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በልደታ ክፍለ ከተማ የተገነባውን ባለ 13 ወለል የአስተዳደር ሕንጻ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል። ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ዛሬ ባለ 13 ወለል የልደታ ክፍለከተማ አስተዳደር ሕንፃ ግንባታን አጠናቅቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ሲሉ አስፍረዋል።   ዘመኑን የሚመጥን የስራ አካባቢ ለመፍጠር በተለያዩ አካባቢዎች ተበታትነው ሲሰጡ የነበሩትን አገልግሎቶች ወደ አንድ ማእከል በማሰባሰብ አገልግሎት የሚያሳልጥ ፣ ለአካል ጉዳተኞችም ምቹ፣ የአገልጋይና የተገልጋይ እንግልት የሚቀንስ፣ ስማርት ሲቲን የመፍጠር ግባችንን ለማሳካት የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ተካተውበት የተገነባ ነው ብለዋል። በውስጡ 120 ቢሮዎችን ጨምሮ እያንዳንዳቸው 1ሺ 500 እና 500 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ሁለት የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ በቂ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ ጂምናዚየም፣ የሕፃናት ማቆያና መጫወቻ ቦታ እና መሰል መገልገያዎች ተሟልተዉለታል ሲሉም ገልጸዋል። በተጨማሪ ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት በጥራት ገንብተን ያጠናቀቅነው ይህ ህንፃ ወጪን በመቆጠብ ከዚህ በፊት ለቢሮ ኪራይ የምናውለውን ሀብት በማስቀረት ለልማት እንድናውል ያስችለናል ብለዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Jan 16, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ዙሪያ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንና በቀጣናው ሰላም ማስከበር ላይ ያላት ሚና እውቅና እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉንም ገልፀዋል። የባህር በር ጥያቄ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲረዳ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አንስተዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው ሀገራት ጋር ሁለንተናዊ ትስስሯን ለማጠናከር የሰራችበት ጊዜ እንደነበርም ጠቁመዋል፡፡ ለአብነትም ኢትዮጵያንና ደቡብ ሱዳንን የሚያገናኘውን የመንገድ ግንባታ ስምምንት ጨምሮ ኢትዮጵያ ለኬኒያ የምትልከውን የኤሌክትሪክ መጠን ለመጨመር ስምምነት ላይ መደረሱን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቁ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች መፈጸማቸውን ጠቁመው ከ128 በላይ የከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት እና ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ32 ሺህ 918 በላይ ዜጎች ወደ ሀገር መመለሳቸውን ተናግረዋል። ከአጎራባች ሀገራት ጋር ያለው የሁለትዮሽና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል። የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ቀደመው ለመመለስ ትልቅ መደላድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይትም ሁሉቱም ሀገራት በሙሉ ውክልና ሚሲዮኖቻቸውን ዳግም ወደ ስራ ማስገባት እንደሚጀምሩ መስማማታቸውንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ሶስተኛውን የፖለቲካ ምክክር ማካሄዳቸውን ነው የገለጹት፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካሄደው ምክክር አገራቱ በግብርና፣ ማዕድን፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፎች ያላቸው ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ፖለቲካ
ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Jan 16, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ዙሪያ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንና በቀጣናው ሰላም ማስከበር ላይ ያላት ሚና እውቅና እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉንም ገልፀዋል። የባህር በር ጥያቄ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲረዳ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አንስተዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው ሀገራት ጋር ሁለንተናዊ ትስስሯን ለማጠናከር የሰራችበት ጊዜ እንደነበርም ጠቁመዋል፡፡ ለአብነትም ኢትዮጵያንና ደቡብ ሱዳንን የሚያገናኘውን የመንገድ ግንባታ ስምምንት ጨምሮ ኢትዮጵያ ለኬኒያ የምትልከውን የኤሌክትሪክ መጠን ለመጨመር ስምምነት ላይ መደረሱን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቁ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች መፈጸማቸውን ጠቁመው ከ128 በላይ የከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት እና ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ32 ሺህ 918 በላይ ዜጎች ወደ ሀገር መመለሳቸውን ተናግረዋል። ከአጎራባች ሀገራት ጋር ያለው የሁለትዮሽና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል። የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ቀደመው ለመመለስ ትልቅ መደላድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይትም ሁሉቱም ሀገራት በሙሉ ውክልና ሚሲዮኖቻቸውን ዳግም ወደ ስራ ማስገባት እንደሚጀምሩ መስማማታቸውንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ሶስተኛውን የፖለቲካ ምክክር ማካሄዳቸውን ነው የገለጹት፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካሄደው ምክክር አገራቱ በግብርና፣ ማዕድን፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፎች ያላቸው ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 
Jan 16, 2025 46
አዲስ አበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ዙሪያ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን እና በቀጣናው ሰላም ማስከበር ላይ ያላት ሚና እውቅና እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል። የባህር በር ጥያቄ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲረዳ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አንስተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከቀጣናዊ ሀገራት ጋር ሁለንተናዊ ትስስሯን ለማጠናከር የሰራችበት ጊዜ እንደነበርም ጠቁመዋል፡፡ ለአብነትም ኢትዮጵያንና ደቡብ ሱዳንን የሚያገናኘውን የመንገድ ግንባታ ስምምነት ጨምሮ ኢትዮጵያ ለኬኒያ የምትልከውን የኤሌክትሪክ መጠን ለመጨመር ስምምነት ላይ መደረሱንም አንስተዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቁ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች መፈጸማቸውንም ጠቁመው ከ128 በላይ የከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት እና ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ሺህ 918 በላይ ዜጎች ወደ ሀገር መመለሳቸውን ተናግረዋል። ከአጎራባች ሀገራት ጋር ያለው የሁለትዮሽ እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል። የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ቀደመው ለመመለስ ትልቅ መደላድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይትም ሁሉቱም ሀገራት በሙሉ ውክልና ሚሲዮኖቻቸውን ዳግም ወደ ስራ ማስገባት እንደሚጀምሩ መስማማታቸውንም ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ሶስተኛውን የፖለቲካ ምክክር ማካሄዳቸውን ነው የገለጹት፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካሄደው ምክክር አገራቱ በግብርና፣ ማዕድን፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፎች ያላቸው ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር የሚግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡    
ኢትዮጵያና ሶማሊያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መጠናከር ከአገራቱ ባለፈ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም አለው
Jan 16, 2025 50
አዲስ አበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ሶማሊያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መጠናከር ከአገራቱ ባለፈ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም እንዳለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተገናኝተው የሁለትዮሽ ምክክር ማድረጋቸው ይታወሳል። ሃገራቱ በአንካራው ስምምነት መሠረት የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ፀጋ ሁለቱ ኢትዮጵያና ሶማሊያ የቆየ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እላቸው ብለዋል። ስምምነቱ የሀገራቱን ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ የቀጣናውን ሰላም ለማረጋገጥ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወትም ጠቁመዋል። እንዲሁም ቀጣናውን ከማረጋጋት ባለፈ ለዘመናት የነበረውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚረዳ ነው ያስታወቁት። በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ የዲፕሎማሲና የመደራደር አቅሟን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ያሳየችበት መሆኑንም ነው የገለጹት። ሁለቱ አገራት በማህበራዊ ጉዳይ በኢኮኖሚና በኢንቨስትመንት ዙሪያ የነበራቸውን የቆየ ግንኙነት ለማሳደግ መስማማታቸው ህዝባቸውን ይበልጥ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ነው የገለጹት። ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከሁሉም ሀገራት ጋር ሰላማዊ በሆነ መንገድ ግንኙነቷን የማሳደግ ፍላጎት እንዳላት ያሳየችበትና ዲፕሎማሲያዊ የበላይነት የተቀዳጀችበት መሆኑን ነው አቶ ፍቃዱ ያነሱት።   የኢንስቲትዩቱ መሪ ተመራማሪ ጥላሁን ተፈራ ( ዶ/ር ) በበኩላቸው እንደገለጹት፥ ሀገራቱ ከዲፕሎማሲ ባሻገር ያላቸውን ዘርፈ ብዙ የኢኮኖሚ ግንኙነት ለማሳደግ መስማማታቸው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሽብርተኝነትን ጨምሮ የሚታዩ ስጋቶችን በጋራ ለመከላከል የሁለቱ ሀገራት ስምምነት በእጅጉ እንደሚጠቅም ነው ያነሱት። ሁለቱ ሀገራት በአንካራ ያደረጉት ስምምነት የቀጣናውን ሰላም የማይፈልጉ ኃይሎችን ዕኩይ ተልዕኮ ያከሸፈ መሆኑንም መሪ ተመራማሪው ገልፀዋል። ሀገራቱ ጥር 3 ቀን 2017 ዓም በአዲስ አበባ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙታቸውን ለማደስ ስምምነት ማድረጋቸው በአንካራ የተደረገውን ስምምነት እንዲፀና የሚያደርግ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አማካኝነት በመሃከላቸው ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት በውይይት ለመፍታት የሚያስችል ስምምነት ማድረጋቸው ይታወቃል።
ባለፉት ስድስት ወራት በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ከ32ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
Jan 16, 2025 71
አዲስአበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ32ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገር መመለስ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፥ በወቅታዊ የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ዙሪያ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የሚኒስቴሩን የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም፣ የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ፣ የኢትዮ-ሶማሊያ ግንኙነት እና ሰሞኑን ከአዘርባጃን ልዑካን ጋር የተደረገውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የተመለከቱትን ጉዳዮች አንስተዋል። በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው ሀገራት ጋር ሁለንተናዊ ትስስሯን ለማጠናከር የሰራችበት መሆኑንም ገልጸዋል። ለአብነትም ኢትዮጵያን እና የደቡብ ሱዳንን የሚያገናኘው የመንገድ ግንባታ ስምምነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለኬኒያ የምትልከውን የኤሌክትሪክ መጠን ለመጨመር ስምምነት ላይ መደረሱንም አንስተዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቁ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች መፈጸማቸውንም ጠቁመዋል። ከ128 በላይ የከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት እና ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ሺህ 918 በላይ ዜጎች ወደ ሀገር መመለሳቸውን ተናግረዋል። ከአጎራባች ሀገራት ጋር ያለው የሁለትዮሽ እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል። የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ቀደመው ለመመለስ ትልቅ መደላድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል።      
ፖለቲካ
ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Jan 16, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ዙሪያ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንና በቀጣናው ሰላም ማስከበር ላይ ያላት ሚና እውቅና እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉንም ገልፀዋል። የባህር በር ጥያቄ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲረዳ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አንስተዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው ሀገራት ጋር ሁለንተናዊ ትስስሯን ለማጠናከር የሰራችበት ጊዜ እንደነበርም ጠቁመዋል፡፡ ለአብነትም ኢትዮጵያንና ደቡብ ሱዳንን የሚያገናኘውን የመንገድ ግንባታ ስምምንት ጨምሮ ኢትዮጵያ ለኬኒያ የምትልከውን የኤሌክትሪክ መጠን ለመጨመር ስምምነት ላይ መደረሱን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቁ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች መፈጸማቸውን ጠቁመው ከ128 በላይ የከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት እና ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ32 ሺህ 918 በላይ ዜጎች ወደ ሀገር መመለሳቸውን ተናግረዋል። ከአጎራባች ሀገራት ጋር ያለው የሁለትዮሽና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል። የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ቀደመው ለመመለስ ትልቅ መደላድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይትም ሁሉቱም ሀገራት በሙሉ ውክልና ሚሲዮኖቻቸውን ዳግም ወደ ስራ ማስገባት እንደሚጀምሩ መስማማታቸውንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ሶስተኛውን የፖለቲካ ምክክር ማካሄዳቸውን ነው የገለጹት፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካሄደው ምክክር አገራቱ በግብርና፣ ማዕድን፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፎች ያላቸው ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 
Jan 16, 2025 46
አዲስ አበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ዙሪያ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ስድስት ወራት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አመርቂ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን እና በቀጣናው ሰላም ማስከበር ላይ ያላት ሚና እውቅና እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል። የባህር በር ጥያቄ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲረዳ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አንስተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከቀጣናዊ ሀገራት ጋር ሁለንተናዊ ትስስሯን ለማጠናከር የሰራችበት ጊዜ እንደነበርም ጠቁመዋል፡፡ ለአብነትም ኢትዮጵያንና ደቡብ ሱዳንን የሚያገናኘውን የመንገድ ግንባታ ስምምነት ጨምሮ ኢትዮጵያ ለኬኒያ የምትልከውን የኤሌክትሪክ መጠን ለመጨመር ስምምነት ላይ መደረሱንም አንስተዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቁ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች መፈጸማቸውንም ጠቁመው ከ128 በላይ የከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት እና ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ሺህ 918 በላይ ዜጎች ወደ ሀገር መመለሳቸውን ተናግረዋል። ከአጎራባች ሀገራት ጋር ያለው የሁለትዮሽ እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል። የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ቀደመው ለመመለስ ትልቅ መደላድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይትም ሁሉቱም ሀገራት በሙሉ ውክልና ሚሲዮኖቻቸውን ዳግም ወደ ስራ ማስገባት እንደሚጀምሩ መስማማታቸውንም ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ሶስተኛውን የፖለቲካ ምክክር ማካሄዳቸውን ነው የገለጹት፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካሄደው ምክክር አገራቱ በግብርና፣ ማዕድን፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፎች ያላቸው ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር የሚግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡    
ኢትዮጵያና ሶማሊያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መጠናከር ከአገራቱ ባለፈ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም አለው
Jan 16, 2025 50
አዲስ አበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ሶማሊያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መጠናከር ከአገራቱ ባለፈ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም እንዳለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተገናኝተው የሁለትዮሽ ምክክር ማድረጋቸው ይታወሳል። ሃገራቱ በአንካራው ስምምነት መሠረት የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ፀጋ ሁለቱ ኢትዮጵያና ሶማሊያ የቆየ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እላቸው ብለዋል። ስምምነቱ የሀገራቱን ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ የቀጣናውን ሰላም ለማረጋገጥ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወትም ጠቁመዋል። እንዲሁም ቀጣናውን ከማረጋጋት ባለፈ ለዘመናት የነበረውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚረዳ ነው ያስታወቁት። በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ የዲፕሎማሲና የመደራደር አቅሟን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ያሳየችበት መሆኑንም ነው የገለጹት። ሁለቱ አገራት በማህበራዊ ጉዳይ በኢኮኖሚና በኢንቨስትመንት ዙሪያ የነበራቸውን የቆየ ግንኙነት ለማሳደግ መስማማታቸው ህዝባቸውን ይበልጥ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ነው የገለጹት። ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከሁሉም ሀገራት ጋር ሰላማዊ በሆነ መንገድ ግንኙነቷን የማሳደግ ፍላጎት እንዳላት ያሳየችበትና ዲፕሎማሲያዊ የበላይነት የተቀዳጀችበት መሆኑን ነው አቶ ፍቃዱ ያነሱት።   የኢንስቲትዩቱ መሪ ተመራማሪ ጥላሁን ተፈራ ( ዶ/ር ) በበኩላቸው እንደገለጹት፥ ሀገራቱ ከዲፕሎማሲ ባሻገር ያላቸውን ዘርፈ ብዙ የኢኮኖሚ ግንኙነት ለማሳደግ መስማማታቸው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሽብርተኝነትን ጨምሮ የሚታዩ ስጋቶችን በጋራ ለመከላከል የሁለቱ ሀገራት ስምምነት በእጅጉ እንደሚጠቅም ነው ያነሱት። ሁለቱ ሀገራት በአንካራ ያደረጉት ስምምነት የቀጣናውን ሰላም የማይፈልጉ ኃይሎችን ዕኩይ ተልዕኮ ያከሸፈ መሆኑንም መሪ ተመራማሪው ገልፀዋል። ሀገራቱ ጥር 3 ቀን 2017 ዓም በአዲስ አበባ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙታቸውን ለማደስ ስምምነት ማድረጋቸው በአንካራ የተደረገውን ስምምነት እንዲፀና የሚያደርግ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አማካኝነት በመሃከላቸው ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት በውይይት ለመፍታት የሚያስችል ስምምነት ማድረጋቸው ይታወቃል።
ባለፉት ስድስት ወራት በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ከ32ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
Jan 16, 2025 71
አዲስአበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ32ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገር መመለስ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፥ በወቅታዊ የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ዙሪያ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የሚኒስቴሩን የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም፣ የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ፣ የኢትዮ-ሶማሊያ ግንኙነት እና ሰሞኑን ከአዘርባጃን ልዑካን ጋር የተደረገውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የተመለከቱትን ጉዳዮች አንስተዋል። በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከቀጣናው ሀገራት ጋር ሁለንተናዊ ትስስሯን ለማጠናከር የሰራችበት መሆኑንም ገልጸዋል። ለአብነትም ኢትዮጵያን እና የደቡብ ሱዳንን የሚያገናኘው የመንገድ ግንባታ ስምምነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለኬኒያ የምትልከውን የኤሌክትሪክ መጠን ለመጨመር ስምምነት ላይ መደረሱንም አንስተዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስጠበቁ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች መፈጸማቸውንም ጠቁመዋል። ከ128 በላይ የከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት እና ውይይቶች መካሄዳቸውንም አንስተዋል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ሺህ 918 በላይ ዜጎች ወደ ሀገር መመለሳቸውን ተናግረዋል። ከአጎራባች ሀገራት ጋር ያለው የሁለትዮሽ እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል። የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ቀደመው ለመመለስ ትልቅ መደላድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል።      
ማህበራዊ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 225 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተፋሰስ ልማት ስራ ይካሄዳል-የግብርና ቢሮ
Jan 16, 2025 35
ቦንጋ፤ጥር 8/2016 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በዘንድሮ የበጋ ወቅት 225 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ልማት ለማካሄድ የንቅናቄ ስራ መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ውብሸት ዘነበ ለኢዜአ እንደገለፁት፥ በክልሉ ባለፉት ሶስት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ተራቁቶ የነበረ መሬት አገግሞ ለእርሻ ስራ መዋል ጀምሯል። በለማው ስፍራ ወጣቶች ተደራጅተው በፍራፍሬና ንብ ማነብ ስራ ላይ ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዘንድሮም ይህን ስራ አጠናክሮ ለማስቀጠል የንቅናቄ ስራ መጀመሩንና ቅድመ ዝግጅት በመደረግ ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ለ30 ቀናት የሚቆየው የዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ እንደ ክልል ጥር 22 በይፋ እንደሚጀመርና ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ለማሳተፍ መታቀዱን ገልጸዋል። በዘንድሮ የበጋ ወቅት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በተለዩ 1 ሺህ 100 ንዑስ ተፋሰሶች 225 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ልማት ስራ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። ስራውን ውጤታማ ለማድረግ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት፣ለልማቱ የሚሆኑ መሳሪያዎችና የሚሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመለየት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል። “ባለፉት ዓመታት የተገኙ ተሞክሮዎችን በማስፋትና ጉድለቶችን በማረም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የተጠናከረ ስራ ይሰራል” ብለዋል። ባለፈው ዓመት በበጋ የአፈርና ውሃ ጥበቃ የተፋሰስ ልማት ከ1 ሺህ በሚበልጡ ንዑስ ተፋሰሶች ለከ217 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ማልማት መቻሉን አስታውሰዋል።  
የጥምቀት በዓልን ፍቅርን፣ትህትናንና አብሮነትን በሚያንጸባርቅ መልኩ በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው- ብጹዕ አቡነ ሩፋኤል
Jan 16, 2025 30
ጋምቤላ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፡- የጥምቀት በዓልን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ አንድነትን፣ ፍቅርን፣ ትህትናንና አብሮነትን በሚያንጸባርቅ መልኩ በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ብጹዕ አቡነ ሩፋኤል ገለጹ። የጋምቤላ፣የቤንሻንጉል፣ የቄለም ወለጋ፣ የሆሮ ጉድሩ ወለጋ፣የምዕራብና የምስራቅ ወለጋና የደቡብ ሱዳን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ሩፉኤል ለጥምቀት በዓል እየተደረገ ያለውን ዝግጅት አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። በዚሁ መግለጫ እንዳመለከቱት፤በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው የጥምቀት በዓል የሕዝቦች አንድነትን፣ ፍቅርን፣ ትህትናንና አብሮነትን በሚያንጸባርቅ መልኩ በድምቀት ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ነው። በጋምቤላ እና በቤኒሻንጉል ክልሎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ፣ ሆሮ ጉድሩ ፣ ምዕራብና ምስራቅ ወለጋ በዓሉን በድምቀት ለማክበር የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ ማክበሪያ ቦታዎችን የማጽዳትና ማስዋብ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። በደቡብ ሱዳንም በጁባ፣ በማላከልና በናስራ አካባቢዎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በዓሉን ለማክበር በዝግጅት ላይ መሆናቸውንና ወደ አካባቢውም አገልጋዮች መላካቸውን ጠቅሰዋል። "ጥምቀት ሰማይና ምድርን የፈጠረው አምላካችን፣ጌታችን ና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍጡሩ መጥምቁ ዮሃንስ እራሱን ዝቅ አድርጎ የተጠመቀበት የትህትና በዓል ነው’’ ብልዋል። ከዚህም ምዕመኑ የሚወሰደው ትምህርት ጥምቀት የትህትናን፣ የፍቅርን፣ የአንድነትን የአብሮነት ተምሳሌት የሚንፀባረቅበት ክብረ በዓል መሆኑን ነው ብለዋል። እንዲሁም የጥምቅት በዓል ያለው ለሌለው የሚያካፍልበት እና የተቸገሩ ወገኖችን የሚደግፉበት ታላቅ የአደባባይ በዓል መሆኑንም ገልጸዋል። በተጨማሪ በዓሉ ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ ቱሪስቶችና ለዓለም ማህበረሰብ የኢትዮጵያን ህዝብ ፍቅርን ፣ትብብርን፣ትህትናንና አንድነትን የሚያሳይበት በዓል መሆኑን ተናግረዋል። በዓሉ ሃይማኖታዊ ይዘቱና ሥርዓቱን ጠበቀ መንገድ ለማክበር ምዕመኑ ከዝግጅቱ ጀምሮ በትብብርና በአንድነት እንዲሰራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ከመዲናዋ የተውጣጡ ወጣቶች በጃንሜዳ የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ስፍራን የማጽዳት መርሃ ግብር አካሄዱ
Jan 16, 2025 39
አዲስ አበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ ከተለያዩ አከባቢዎች የተውጣጡ ወጣቶች በጃንሜዳ የከተራና ጥምቀት በዓል በሚከበርበት ስፍራ የጽዳት መርሃ ግብር አከናውነዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከምታከብራቸው ኃይማኖታዊ በዓላት መካከል የከተራና ጥምቀት በዓል ይጠቀሳሉ። በዓሉን በመጪዎቹ ቅዳሜ እና እሁድ በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች ለማክበር ቅድመ ዝግጅት እየተካሄደ እንደሆነም ይታወቃል። ዛሬ በማለዳው የአዲስ አበባ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መልኩ የከተራና የጥምቀት በዓል በድምቀት ከሚከበርባቸው ቦታዎች አንዱ የሆነውን የጃንሜዳ ታቦት ማደሪያን አጽድተዋል። በጽዳት መርሃ ግብሩ ላይ ከተሳተፉ በጎ ፈቃደኞች መካከል ቤተልሄም እንድሪስ እና አቶ ሀሰን ከበደ፥ ኢትዮጵያ በርካታ ሃይማኖቶች በመከባበርና በአብሮነት የሚኖሩባት ሀገር መሆኗን ገልጸዋል።   ሃይማኖታዊ በዓላት በሚከበሩበት ወቅትም እርስ በርስ በመጠያየቅ ክብረ በዓላት የሚከበሩባቸውን ስፍራዎች በጋራ በማጽዳትና በማስዋብ አብሮነትን የሚያሳዩበት መሆኑን ተናግረዋል። ሌላው የጽዳት ዘመቻው ተሳታፊ ስንታየሁ ስርጋዊ፥ የከተራና ጥምቀት በዓል ማክበሪያ ስፈራን ከማጽዳት ባለፈ በመዲናዋ በዓሉ ተከብሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ የማስተባበር ስራን በመስራት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ተወካይ አቶ ጤናዬ ታምሩ፥ በመርሃ ግብሩ ላይ እንዳሉት የከተራ እና የጥምቀት በዓል በድምቀት እንዲከበር የጽዳት ዘመቻው መካሄዱን ተናግረዋል።   በመዲናዋ ሃይማኖታዊ በዓላት ሲከበሩ በጎ ፈቃደኞችን ያሳተፈ የፀዳት ዘመቻ ማከናወን እየተለመደ የመጣ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸው፥ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶችና ወጣቶች መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ራምላ ከድር፥ በበኩላቸው ለሀገር መልካም ገጽታ ግንባታ ሃይማኖታዊ በዓላት የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ጥምቀት በዩኔስኮ በማይዳሰስ የባህል ቅርስነት ከተመዘገቡ አለም አቀፍ ሀብቶች መካከል አንዱ በመሆኑ በዓሉ በድምቀት ከሚከበርበት ስፍራዎች አንዱ በሆነው ጃንሜዳን የማጽዳት ስራ መከናወኑን ገልጸዋል። በዓሉ ሃይማኖታዊ ቱውፊቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ሁሉም የበኩሉን ሚና ሊወጣ እንደሚገባውም አመላክተዋል።
በአዳማ የበዓል የባህል አልባሳት በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት ለገበያ ቀርበዋል
Jan 16, 2025 41
አዳማ ፤ ጥር 8 / 2017(ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ የጥምቀት ክበረ በዓልን አስመልክቶ በአዳዲስ ዲዛይኖች የተሰሩ የባህል አልባሳት በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት ለገበያ መቅረባቸውን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነጋዴዎችና ሸማቾች አስታወቁ። በአዳማ የሀገር ባህል አልባሳት በስፋት ለገበያ ካቀረቡ ነጋዴዎች መካከል ወይዘሮ ዮዲት መለሰ በሰጡት አስተያየት፤ በሁሉም እድሜ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ባህላዊ አልባሳት በአዳዲስ ዲዛይኖች ተዘጋጅተው ለገበያ ቀርበዋል። የሀገር ባህል አልባሳት በስፋት ከሚለበሱባቸው የአደባባይ በዓላት መካከል ጥምቀት ዋንኛው መሆኑን ጠቅሰው፤ ለባህል አልባሳት አቅራቢ ነጋዴዎችም ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። ጥምቀት ከሌላው ጊዜ የተሻለ ገበያ የሚገኝበት መሆኑን ታሳቢ ያደረገ የአቅርቦት ዝግጅት ማድረጋቸውንም ጠቁመዋል። ለዚህም ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያማከለ አዳዲስ ዲዛይኖችን በመጨመር በርካታ የሴቶችና የወንዶች አልባሳትን አዘጋጅተው ለገበያ ማቅረባቸውን አመልክተዋል። በዚህም ከ1 ሺህ 500 እስከ 4 ሺህ 500 ብር ዋጋ ያላቸው አልባሳት ማቅረባቸውን የሚገልጹት ወይዘሮ ዮዲት፤ ተጠቃሚውም እየሸመት በመሆኑ የተሻለ ገበያ መኖሩን ተናግረዋል። ሌላኛዋ የባህል አልባሳት ነጋዴ ወይዘሮ ዝናሽ አበበ በበኩላቸው፤ ከበአል ቀናት በተጨማሪ በማንኛውም ዝግጅት ወቅት ሊለበሱ የሚችሉ የባህል አልባሳትን አዘጋጅተው ማቅረባቸውን ጠቁመዋል። በተለይ ለጥምቀት በአል በአዳዲስ ዲዛይን በስፋት ለገበያ ማቅረባቸውን ጠቅሰው፤ ከበአሉ ጋር ተያይዞም ተጠቃሚው እንደ አቅሙና ፍላጎቶቱ ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸው ባህላዊ አልባሳት አዘጋጅተው ለገበያ ማቅረባቸውን ተናግረዋል። ለጥምቀት በአል የሀገር ባህል ልብስ ሲገዙ ያገኘናቸው የአዳማ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ አበባ ይሁን፤ ለበአሉ በአዳዲስ ዲዛይኖች የተሰሩ የልጅና አዋቂ አልባሳት በስፋት ገበያ ላይ እንዳሉ ጠቅሰዋል። እሳቸው ለህጻናት ልጆቻቸው የሚሆኑ የባህል አልባሳት ለመሸመት መምጣታቸውን የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዋ፤ የባህል አልባሳት አሁን አሁን በተሻለ መልኩ ለገበያ እየቀረቡ መሆኑ ልጆች ባህላቸውን እያወቁ እንዲያድጉ የሚያደርግ እንደሆነም ተናግረዋል። ለበአሉ በስፋት የሀገር ባህል ልብስ ተዘጋጅቶ መቅረቡ በዓሉን ለማድመቅ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የተናገረው ደግሞ የባህል አልባሳትን ከቤተሰቡ ጋር ሆኖ ሲገዛ ያገኘነው ወጣት ዮሃንስ ዳኙ ነው። የባህል አልባሳት ገበያውና ድባቡ ደስ ይላል የሚለው ወጣቱ፤ ጥምቀትን በድምቀት ለማክበር እና ከባአሉ ባለፈ ለሌሎች ዝግጅት የሚለበስ የባህል ልብስ መግዛታቸውን አውስቷል።              
ኢኮኖሚ
ባንኩ በትግራይ ክልል ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው - አቶ ጌታቸው ረዳ
Jan 16, 2025 37
መቀሌ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትግራይ ክልል ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ግንባር ቀደም አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞችን ቀን ምክንያት በማድረግ ዛሬ በመቀሌ ከተማ ከባለሀብቶች ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል።   በምክክር መድረኩ የተገኙት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ በክልሉ በነበረው ችግር ተቀዛቅዞ የቆየው የኢኮኖሚ እንቀስቃሴ እንዲነቃቃ ባንኩ ያደረገውን አስተዋጽኦ አድንቀዋል። የንግዱ ማህበረሰብ ያለውን የፋይናንስ ፍላጎት እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አጥንቶ የሚሰጠውን በጎ ምላሽና የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይብልጥ እንደሚያጠናክር እምነታቸው መሆኑንም ገልጸዋል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የፋይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ሀላፊ ምህረት በየነ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የክልሉ ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ የንግድ ባንክ ድርሻ የጎላ ነው ብለዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ነጋ ገብረ ስላሴ የተባሉ ባለሀብት በሰጡት አስተያየት፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን አገልግሎት እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።   ሌላው ባለሃብት አቶ መሐሪ ፍስሀ፤ ንግድ ባንኩ ራሱን ለማዘመን እየሰራቸው ያሉት ስራዎች ይበልጥ ሊያጠናክር ይገባል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመቀሌ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ልሳነወረቅ በበኩላቸው ባንኩ የሚተማመንባቸው ደንበኞች በክልሉ መኖራቸውን ገልፀዋል። ንግድ ባንኩ የብድር አገልግሎትን ለማሻሻልና አገልግሎቱን ለማዘመን በመስራት ላይ መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይም አገልግሎቱን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመቀሌ ዛሬ ባዘጋጀው የደንበኞች አገልግሎት መድረክ በተለያዩ የልማትና የንግድ ስራዎች የተሰማሩ ባለሀብቶች ተሳትፈዋል።
በኦሮሚያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚጠጉ የወተት ላሞች በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ ተዳቅለዋል - የክልሉ ግብርና ቢሮ
Jan 16, 2025 37
አዳማ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚጠጉ የወተት ላሞች በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ መዳቀላቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የእንስሳት ማሻሻያና ልማት ዳይሬክተር አቶ ደምሴ ኩምሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የወተት ላሞች የዝሪያ ማሻሻልና የእንስሳት ሀብት ልማት ኢንሼቲቭ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።   የወተት ሀብት ልማትን በመጨመር የወተትና ወተት ተዋፅዖ ወጤቶች በበቂ ደረጃ ተደራሽ በማድረግ ስርዓተ ምግብን ለማሻሻል የተጀመረውን የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በእስካሁኑ ሂደት የሀገረ ሰብ ላሞች በአማካይ በቀን 1 ነጥብ 5 ሊትር ወተት እንደሚገኝ የጠቀሱት ዳይሬክተሩ በተሻሻሉ የወተት ላሞች የወተት ምርቱን በቀን ወደ 12 ነጥብ 5 ለማሳደግ መታቀዱን ገልጸዋል። በክልሉ ባለፈው ዓመት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የወተት ላሞች በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ የተዳቀሉ ሲሆን በዚህ ዓመት 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን የወተት ላሞችን በመደበኛና በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ የማዳቀል ስራ እየተካነወነ ነው ብለዋል።   በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት በሁሉም የክልሉ ዞኖች በዘመቻ መልክ በተሰራው ስራ በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ የወተት ላሞች ማዳቀል መቻሉን ጠቅሰዋል። በዚህም የወተት ምርት ልማትና እድገት እየጨመረ መሆኑን ጠቅሰው በክልሉ በዘርፉ የተቀመጠውን የሌማት ትሩፋት ለማሳካት የተሻለ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የወተት መንደሮችን የማደራጀት ስራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቅሰው በወተት ላሞች ዝርያ ማሻሻያ የተቀመጠውን ግብ ማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ የሆኑ የሀዋሳ ዙሪያ አርሶ አደሮች
Jan 16, 2025 39
ሀዋሳ ጥር 8/2017 (ኢዜአ):- በአካባቢያቸው የተገነቡ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች በልማቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ አርሶ አደሮች ገለጹ። በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የጋሎ አርጊሳ ቀበሌው አርሶ አደር ታምራት ሄርቃሎና አርሶ አደር ሽንኩራ ሹናለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ ተመርቆ ወደ ሥራ የገባውን የኤጀርሳ መስኖ ፕሮጀክት ተጠቅመው 1 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት የተለያዩ የአትክልትፋ ፍራፍሬ ሰብሎችን በመስኖ እያለሙ ነው።     በመስኖ ልማት የሥራ ዕድል የተፈጠረለት ወጣት ታደሰ ህዝቄል በበኩሉ፤ ሰርቶ ያገኘውን ገንዘብ በመቆጠብ ላሞችን መግዛቱን ጠቁሞ በቀጣይ በመስኖ ልማት የመሰማራት ዕቅድ እንዳለው ገልጿል። የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሃይሉ ሁሪሳ በበኩላቸው በወረዳው ያለውን የውሃ አቅም በመጠቀም ከ5 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ በማልማት 12 ሺህ 500 አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በወረዳው ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ሦስት ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ዘንድሮ ወደስራ መግባታቸውን የገለጹት ደግሞ የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ገጠር ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ አሰፋ ፎና ናቸው። በሦስቱም የመስኖ ፕሮጀክቶች የመስኖ ልማት ሥራው እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው በልማቱ የአርሶ አደሩን ገቢ ከማሳደግ ባለፈ ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የልደታ ክፍለ ከተማን የአስተዳደር ሕንፃ መርቀው ከፈቱ
Jan 16, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በልደታ ክፍለ ከተማ የተገነባውን ባለ 13 ወለል የአስተዳደር ሕንጻ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል። ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ዛሬ ባለ 13 ወለል የልደታ ክፍለከተማ አስተዳደር ሕንፃ ግንባታን አጠናቅቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ሲሉ አስፍረዋል።   ዘመኑን የሚመጥን የስራ አካባቢ ለመፍጠር በተለያዩ አካባቢዎች ተበታትነው ሲሰጡ የነበሩትን አገልግሎቶች ወደ አንድ ማእከል በማሰባሰብ አገልግሎት የሚያሳልጥ ፣ ለአካል ጉዳተኞችም ምቹ፣ የአገልጋይና የተገልጋይ እንግልት የሚቀንስ፣ ስማርት ሲቲን የመፍጠር ግባችንን ለማሳካት የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ተካተውበት የተገነባ ነው ብለዋል። በውስጡ 120 ቢሮዎችን ጨምሮ እያንዳንዳቸው 1ሺ 500 እና 500 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ሁለት የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ በቂ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ ጂምናዚየም፣ የሕፃናት ማቆያና መጫወቻ ቦታ እና መሰል መገልገያዎች ተሟልተዉለታል ሲሉም ገልጸዋል። በተጨማሪ ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት በጥራት ገንብተን ያጠናቀቅነው ይህ ህንፃ ወጪን በመቆጠብ ከዚህ በፊት ለቢሮ ኪራይ የምናውለውን ሀብት በማስቀረት ለልማት እንድናውል ያስችለናል ብለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ርዕደ መሬት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ሁሉን አቀፍ የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jan 16, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ ርዕደ መሬት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ሁሉን አቀፍ የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የርዕደ መሬት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዝግጁነታችንና የምላሽ ሁኔታችን ባለን ቴክኖሎጂ፣ ሳይንሳዊ ምርምር፣ ትንተናና የትንበያ አቅም የሚወሰን ነው ብለዋል።   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ የስፔስ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት ዛሬ ዛሬ በተደረገው ጉብኝት በርዕደ መሬት ነክ ሳይንሳዊ ምርምር አበረታች ስራዎች ለመመልከት መቻሉን ተናግረዋል። ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በርዕደ መሬት ክስተት ዙሪያ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ተጠናከረ ተግባር መገባቱን ጠቁመዋል።   አደጋው በተከሰተባቸው አካባቢዎች የመሠረተ-ልማት፣ የጊዜያዊ መጠለያ፣ የሰብአዊ ድጋፍ፣ የሳይንሳዊ ትንተና እና ትንበያ ቡድኖችን በማደራጀት በዕቅድ ላይ የተመሰረተ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥት የአጭርና የረጅም ጊዜ ሀገራዊ ዝግጁነትን ለማጎልበት የጥናትና ምርምር ተቋማት ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂና ብቁ የሰው ኃይል ጠንካራ ቁመና እንዲፈጥሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ተቋማቱ በችግር ፈቺ የፈጠራ ምርቶች ምን ያህል ውጤታማ ሆነዋል?
Jan 15, 2025 49
የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ግብ ችግር ፈቺ የምርምርና የፈጠራ ስራዎችን ዕውን ማድረግ ነው። ዘርፉ የኢንዱስትሪላይዜሽን ጉዞ መስፈንጠሪያ ነው። በተለይም የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀሩ ሀገራዊ ተኪ ምርቶችን በማምረት። በዚህም ተቋማቱ አንድም በምርምርና ፈጠራ ስራዎችን ውጤታማ መሆን፣ አንድም በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ብቁና በቂ የሰው ኃይል የማፍራት ግብ ሰንቀው ይሰራሉ። ተቋማቱ የፈጠራ ውጤቶችን በተግባር ከማዋል በዘለለ በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ረገድም አይተኬ ሚና ይጫወታሉ። በኢትዮጵያም ይህ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቶት በርካታ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ተቋቁመው ወደስራ ገብተዋል። ለመሆኑ ተቋማቱ በችግር ፈቺ የፈጠራ ምርቶች ምን ያህል ውጤታማ ሆነዋል የሚለውን ኢዜአ የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ለአብነት ቃኝቷል። የኮሌጁ መምህር ወርቁ ፈንታሁን እና ተማሪ ዳግም ጋርጦ ኮሌጁ እና የኮሌጁ ሰልጣኞች ቁልፍ ግባቸው ችግር ፈቺነት ነው ብለው ያምናሉ። መምህሩና ደቀ መዝሙሩም በቅርብ የተመለከቱትን ችግር የሚፈታ የፈጠራ ስራ ለማውጣት ወሰነው ወደስራ ገብተዋል። መምህር ወርቁ ከሩቅ ሳይሆን ከቅርብ ችግር ተነስተው የእንስሳት መኖ ማቀነባበርያ ማሽን መስራት ችለዋል። ይሄውም በሚያስተምሩበት የጀኔራል ዊንጌት ኮሌጅ የሚካሄደውን የከብት እርባታና ማድለብ ስራ ጋር ተያይዞ የተፈጠረው የመኖ እጥረት የመኖ ማቀነባበሪያ ለማምረት ምክንያት ሆኗቸዋል። ፈጠራቸውም የኮሌጁን ችግር አቃሏል። ይኼውም ኮሌጁ ለእንስሳት መኖ ግዢ የሚያወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ ማስቀረታቸው ነው። መምህር ወርቁ እንደሚሉት ማሽኑ ከውጭ ቢገባ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚጠይቅ ሲሆን እርሳቸው ግን በ400 ሺህ ብር ብቻ ሀገር ውስጥ መተካት ችለዋል። ማሽናቸው በሰዓት 4 ኩንታል፤ በቀን ደግሞ 15 ኩንታል መኖ ያቀነባበራል። ከአዋጭነት አኳያም በወር እስከ 100 ሺህ ብር ትርፍ ያስገኛል ይላሉ። የመኖ ማቀነባበርያ ማሽኑን በብዛት አምርቶ በአዲስ አበባ በከተማ ግብርና ለተሰማሩ አካላት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ይገልጻሉ። የኮሌጁ ተማሪ ዳግም ጋርጦ ደግሞ አካል ጉዳተኞችን፣ አቅመ ደካሞችንና ህፃናትን መመገብ የሚያስችል ሮቦት ነው የሰራው። ሮቦቱ ለአንድ ሰው በቀን የሚመገበውን ምግብ እና የሚጠጣውን ውሃ በልኬት በተሰጠው መጠን ልክ ድጋፍ ለሚሹ ህብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችላል። ለህብረተሰቡ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ መስራት ለሀገር ያለውን ወሳኝ ፋይዳ የሚያነሳው ዳግም፤ ለዚህ ደግሞ ለዘርፉ ምቹ ምህዳር ሊፈጠር እንደሚገባ ያነሳል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኖሎጂና የኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ መሀመድ ልጋኔ እንደሚሉት በከተማዋ በሚገኙ 15 የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ብቁና ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ተተኩሯል። ማሰልጠኛ ተቋማት ችግር ፈቺ የምርምርና የፈጠራ ስራዎችን በማውጣት ለሕብረተሰቡ ተደራሽ እያደረጉ እንደሆነም ይገልጻሉ። እስካሁንም ከውጭ ይገቡ የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ጥሬ ግብዓቶች በመጠቀም ተኪ ምርቶችን በማምረት ምሳሌ የሆኑ ኮሌጆች እንዳሉ የጀኔራል ዊንጌትን ለአብነት ይጠቅሳሉ።
አገልግሎቱ አሰራሩን ይበልጥ ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው -ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት
Jan 14, 2025 64
አዲስ አበባ፤ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሰራሮቹን ይበልጥ ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቢዝነስ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል። ዋና ዳይሬክተሯ፥ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቢዝነስ ልዑክ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል። ዋና ዳይሬክተሯ በዚህ ወቅትም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑን ገልፀው፥ የሚሰጡ አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነና ስራዎችንም ለማዘመን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሁለቱ አካላት ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ ልዑኩ ያለውን ልምድና ተሞክሮ በሚያጋራበት እንዲሁም በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ አባላት በበኩላቸው፥ ተቋሙ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ በትብብር ለመስራት ፋላጐት እንዳላቸው መግለጻቸውን ከአገልግሎቱ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮ ቴሌኮምና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ''ስማርት ኮርት ሲስተም" ን ለመተግበር የሚያስችል የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ
Jan 14, 2025 75
ባህርዳር፤ ጥር 6/2017(ኢዜአ)፡-ኢትዮ ቴሌኮምና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ"ስማርት ኮርት ሲስተም" ን በክልሉ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አለምአንተ አግደው ናቸው። ''ስማርት ኮርት ሲስተም" የክስ መዝገቦች አያያዝን ማሻሻል፣ በቪዲዮ የተደገፈ የዳኝነት አገልግሎት መስጠት እንዲሁም ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው ፋይል እንዲከፍቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑና ሌሎች የዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሻል ስርዓት መሆኑ ተመልክቷል።   የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ መንግስታዊ አገልግሎትን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ዘመኑን የሚመጥን ዲጅታል ቴክኖሎጂን መጠቀም ግድ የሚልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል። ''ዛሬ የፍትህ ስርዓትን በቴክኖሎጂ አግዘን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር የጋራ ስምምነት በማድረጋችን ደስ ብሎኛል'' ብለዋል። ''የተጣለብንን ኃላፊነት በብቃትና በጥራት ለመወጣት በቁርጠኝነት እንሰራለን'' ሲሉ ተናግረው ኩባኒያው በየተቋማቱ ለዜጎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማዘመን አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አለምአንተ አግደው በበኩላቸው፤ በክልሉ የፍርድ ቤቶችን አሰራር ለማሻሻል እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ፍርድ ቤቶች ስራቸውን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው ካልሰሩ አገልግሎትን ቀልጣፋና ተደራሽ ማድረግ እንደማይቻል ገልፀው፤ የዳኝነትና የፍትህ ስርዓቱን ቀልጣፋ ለማድረግ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ተደራሽ ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም በክልሉ የሚገኙ ፍርድ ቤቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማስተሳሰር የተቀላጠፈ የዳኝነት አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ''የስማርት ኮርት'' አገልግሎት በተለይ ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው ፋይል እንዲከፍቱ ትልቅ ዕድልን ይዞ የሚመጣ ከመሆኑም በላይ የተቀላጠፈ የዳኝነት አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል። በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይም የኢትዮ ቴሌኮምና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአመራር አባላት ተገኝተዋል።  
ስፖርት
ባህላዊ ስፖርቶች የአብሮነትና የህብረ ብሄራዊነት መገለጫ ናቸው
Jan 16, 2025 40
አዲስ አበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ "የባህል ስፖርቶች ለህብረ ብሄራዊ አንድነት"በሚል መሪ ሃሳብ ከታህሳስ 26 ቀን 2017 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው 15ኛው ከተማ አቀፍ የባህል ስፖርት ውድድር እና ፌስቲቫል ተጠናቋል። በውድድሩ አስራ አንዱ ክፍለ ከተሞች በዘጠኝ የስፖርት ዓይነቶች የተሳተፉ ሲሆኑ በሁሉቱም ጾታዎች ከ10 ሺህ በላይ ስፖርተኞች ተሳታፊ ሆነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን ፤ባህላዊ ስፖርት ለዛሬው ዘመናዊ ስፖርት መሰረት መሆኑን ነው የገለጹት። ባህላዊ ስፖርትን በህብረተሰቡ ዘንድ ለማጎልበትና ለማስረፅ በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ በማካተት ከትምህርት ቤት ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አሰራሩ ተማሪዎች ከልጅነታቸው አንስቶ ከቀለም ትምህርት ጎን ለጎን ባህላዊ ትውፊታቸውን እንዲያውቁ የሚያግዝ ነው ብለዋል። ባህላዊ ስፖርት የአብሮነትና የህብረ ብሄራዊነት መገለጫ በመሆኑ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥተን ልንሰራበት ይገባል ብለዋል። መርኃ ግብሩ በ22ኛው ሀገር አቀፍ የባህል ፌስቲቫል ላይ አዲስ አበባን ወክለው የሚሳተፉ ስፖርተኞች የተመረጡበት መሆኑን አመላክተዋል ። ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በሁሉም የስፖርት ዓይነቶች 8 ወርቅ ፣ 10 ብር እና 4 ነሃስ በድምሩ 56 ሜዳሊያ በማስመዝገብ ውድድሩን በበላይነት ሲያጠናቅቅ አቃቂ ቃሊቲ ሁለተኛ፣ቦሌ ክፍለ ከተማ ሶስተኛ ሆነዋል። በቡብ፣በፈረስ ጉግስ ፣በፈረሰ ሽርጥ ፣በኩርቦ፣በሻህ ፣በቀስት፣በገበጣ ፣በገና ፣ በትግል በሁሉቱም ፆታ ማካሄድ መቻሉም ተገልጿል ። የዘንድሮውን ውድድር ያዘጋጀው ቦሌ ክፍለ ከተማ ሲሆን ቀጣዩን ውድድር ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እንዲያዘጋጅ ተመርጧል።
የሊጉ የ14ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ 
Jan 16, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2016 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር የመጨረሻ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። የዕለቱ የመጀመሪያ መርሃ ግብር ፋሲል ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡናን ከቀኑ 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ያገናኛል። ፋሲል ከነማ ካለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች በሁለቱ ድል ሲቀናው ሶስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ አራት ግቦችን ሲያስቆጥር ሁለት ግቦች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ16 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ ቡና በሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። ሁለት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ አራት ጎሎችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ ሁለት ግቦችን አስተናግዷል። ኢትዮጵያ ቡና በ16 ነጥብ ተጋጣሚውን በግብ ክፍያ በልጦ 9ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ14ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ መድን ከሃዋሳ ከተማ ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮጵያ መድን ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች ሽንፈት አላስተናገደም። ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ስምንት ጎሎችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ ሶስት ግቦችን አስተናግዷል። ኢትዮጵያ መድን በ20 ነጥብ 5ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ በበኩሉ ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ሁለት ጊዜ ሲሸነፍ ሶስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ አንድ ግብ ብቻ ሲያስቆጥር ሶስት ጎሎች ተቆጥረውበታል። ሃዋሳ ከተማ በ10 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በተያያዘ ዜና ትናንት በተደረጉ የ14ኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 0 ሲረታ ሲዳማ ቡና እና መቀሌ 70 እንደርታ ያደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
ወላይታ ድቻ ወደ አሸናፊነት የተመለሰበትን ድል አስመዝግቧል
Jan 15, 2025 45
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2016 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ያሬድ ዳርዛ በ8ኛው ደቂቃ እና ተቀይሮ የገባው ብስራት በቀለ በ84ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ወላይታ ድቻ ከአምስት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል። በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ድሉን ያገኘው ወላይታ ድቻ በ19 ነጥብ ደረጃውን ከ10ኛ ወደ 7ኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በሊጉ 11ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን 18ኛ ደረጃ ይዟል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሊጉ እስከ አሁንም ምንም ጨዋታ ያላሸነፈ ብቸኛው ክለብ ነው። በተያያዘም ቀን ላይ በተደረገ የ14ኛ ሳምንት ጨዋታ ሲዳማ ቡና እና መቀሌ 70 እንደርታ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በመዲናዋ ባለፉት ስድስት ወራት ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ከ874 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ
Jan 16, 2025 36
አዲስ አበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ ባለፉት ስድስት ወራት ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ከ874 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ አስታወቀ። የኮሪደር ልማቱ ለጽዳት ሽርክና ማህበራት የተሻለ ገቢ እያስገኘ መሆኑም ተገልጿል። በአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ የመልሶ መጠቀምና ዑደት ማዕከል ዳይሬክተር ባዩሽ ታደሰ ለኢዜአ እንደገለፁት፥ ደረቅ ቆሻሻን መልሶ መጠቀምና ዑደት ማድረግ የተሰማሩ ከ336 የሽርክና ማህበራት በየወረዳው ተደራጅተው ስራ እየሰሩ ነው። እነዚህ ማህበራት ባለፉት ስድስት ወራት ከ49ሺህ ቶን በላይ ደረቅ ቆሻሻ በመልሶ መጠቀምና ዑደት ላይ ጥቅም ላይ ማዋላቸውን አመልክተዋል።   በዚህም የጽዳት ሽርክና ማህበራቱ ባለፉት ስድስት ወራት ከ874 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ነው ዳይሬክተሯ የገለጹት። ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ30 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል በኮሪደር ልማቱ ለአረንጓዴ ቦታዎች ልማት የሚውል የተፈጥሮ ማዳበሪያ ፍላጎቱ እየጨመረ መሆኑን ተከትሎ ማህበራቱ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በብዛት እንዲያቀርቡ ዕድል መፍጠሩን ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ጽዳትና ውበት ከማጉላት ባለፈ ማህበራቱን ገቢ እንዲያገኙ ዕድል መፍጠሩንም ነው ያነሱት። በተለይም ወረቀት፣ ካርቶኖችና ሌሎች ተረፈ ምርቶችን በብዛት እንዲያገኙና መልሶ ጥቅም ላይ እንዲያውሉ ማስቻሉን አንስተዋል። በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት 2 ሺህ 580 ቶን የተፈጥሮ ማዳበሪያ አምርተው መሸጥ ችለዋል። ኤጀንሲው በተያዘው በጀት ዓመት አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱንና አሁን ላይ ከዕቅዱ በላይ መከወን መቻሉን አንስተዋል። በቀጣይም የማህበራቱን አቅም ለመገንባትና የገበያ አድማሳቸውን ለማስፋት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል።
ያከናወነው የተፋሰስ ልማት ስራ የመሬት ለምነትን በመጨመር በፍራፍሬና በሰብል ምርት ተጠቃሚ እንድንሆን አስችሎናል-አርሶ አደሮች
Jan 16, 2025 66
አዲስ አበባ፤ጥር 8/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ዓመታት ያከናወኗቸው የተፋሰስ ልማት ስራዎች የመሬት ለምነትን በመጨመር በፍራፍሬና በሰብል ምርት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻሉን አርሶ አደሮች ገለጹ፡፡ የተፋሰስ ልማት ስራው በጎርፍ የተሸረሸሩ መሬቶች እንዲያገግሙ በማስቻል ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አንጻር ትልቅ አበርክቶ አለው፡፡   በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሀገራዊ ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉ ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተወጣጡ አርሶ አደሮች የተፋሰስ ልማት ስራዎች አከባቢያቸውን በተጨባጭ መለወጥ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ዞን አርሶ አደር ተበጄ ጌታሁን እንዳሉትም፤ በአካባቢያቸው በደን መራቆት ምክንያት የአፈር መሸርሸር፣ የምንጮችና ወንዞች ደርቀው እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ችግሩን ለመፍታት የአካባቢው አርሶ አደሮች በጋራ በሰሩት የተፋሰስ ልማት ስራ ዛሬ ላይ አካባቢያቸው ወደ ለምነት መለወጡን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ደርቀው የነበሩ ምንጮች መመለሳቸውን ጠቁመው፥ የአካባቢው አርሶ አደሮች የሙዝ ተክል በማልማት ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ በጎርፍ ተሸርሽሮ የነበረው የእርሻ ማሳቸውም አገግሞ ዛሬ ላይ እንደ በቆሎ፣ በርበሬ እና ሌሎች ልማቶችን በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡   የተፋሰስ ልማት ስራ በመስራታቸው የተራቆተ አካባቢያቸውን መለወጥ መቻላቸውን ገልጸው፤ ምርትና ምርታማነት መጨመሩን የገለጹት ደግሞ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በንቅናቄ ማስጀመሪያው ላይ የተሳተፉ አርሶ አደር ማሪ ጉታ ናቸው፡፡ የተፋሰስ ልማት ስራ ባከናወኑባቸው አካባቢዎች በዓመት ሶስት ጊዜ የእንስሳት መኖ በማጨድ ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የግብርና ባለሙያ አብዲ መሐመድ በገጠር ቀበሌዎች ሲያጋጥሙ የነበሩ የጎርፍና የድርቅ ተጋላጭነትን በዘላቂነት ለማስቀረት የተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ውጤት ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡   ከሲዳማ ክልል ተሳታፊ የሆኑት የግብርና ባለሙያ ደረጀ ተድላ በበኩላቸው ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልምት ስራዎች በጎርፍ ምክንያት ተሸርሽረው ምርት መስጠት ያልቻሉ ማሳዎች ወደ ምርታማነት እንዲመለሱ ማስቻሉን ተናግረዋል። የተፋሰስ ልማቱ የማር እና የፍራፍሬ ምርታማነትን ከመጨመር ባሻገር የሰብል ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡ ባለፉት ስድስት አመታት በተከናወነው የተፋሰስ ልማት 40 ቢሊዮን የሚሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን መትከል የተቻለ ሲሆን በዚህም የሀገሪቱ የደን ሽፋን ከነበረበት 17 ነጥብ 5 በመቶ በታች በአሁኑ ወቅት ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በላይ ማሳደግ ችሏል።
69ኛው የአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም በቀጣይ ሳምንት በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Jan 15, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- 69ኛው አፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም(GHACOF 69) ጥር 12 እና 13 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ፎረሙ የሚካሄደው “የአየር ንብረት አገልግሎት፤ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ክፍተቶችን በጋራ ለመሙላት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና የመተግበሪያ ማዕከል(ICPAC) ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን ፎረሙን እንዳዘጋጀ ተገልጿል። በፎረሙ እ.አ.አ ከማርች እስከ ሜይ 2025 ያለው ቀጠናዊ የአየር ትንበያ ይፋ እንደሚደረግ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ለኢዜአ በላከው መግለጫ አስታውቋል።   እ.አ.አ ከኦክቶበር እስከ ዲሴምበር 2024 የነበረው የአየር ንብረት ትንበያ አፈጻጸም ውይይት እንደሚደረግበትም ገልጿል። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ለመገንባት በመተግበር ላይ ያሉ ስትራቴጂዎች እና የተገኙ ውጤቶች ላይ የተመለከተ ውይይትም ይካሄዳል። በፎረሙ የዘርፉ ተመራማሪዎችን፣ ፖሊሲ አውጪዎችን፣ የልማት አጋሮችንና የዘርፉ ተዋንያንን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ አማራጭ መሆኑ ተመላክቷል። ከዋናው ፎረም አስቀድሞ የአየር ንብረት ትንበያ እና ተጓዳኝ አውደ ጥናቶች እንደሚካሄዱ ኢጋድ አስታውቋል። 68ኛው የአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
የተፋሰስ ልማት ውጤታማነት ማሳያ - ሐረማያ ሃይቅ
Jan 15, 2025 52
ላለፉት 17 ዓመታት ደርቆ የነበረው የሐረማያ ሃይቅ በተሰራ የተፋሰስ ልማትና በተደረገለት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች ወደነበረበት እንዲመለስና የውሃው መጠንም ከዓመት ዓመት እንዲጨምር አስችሏል። በሐረማያና አካባቢው ባሉ ተፋሰሶች ላይ የሚከናወኑ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ስራዎች የአርሶ አደሩንና ወጣቱን ተጠቃሚነት ከማጎልበት አንጻር ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናግረዋል። በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሐረማያ ሃይቅ ተፋሰስ ልማት ፕሮጀክት አስተባባሪና የተፈጥሮ ሃብት አጠቃቀም መምህር ዲኔ ረሺድ እንደገለፁት፤ የአየር ንብረት ለውጥ ችግርን ለመቋቋም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው። ባለፉት ዓመታት በአካባቢው የተከናወኑት የአፈርና ውሃ እንዲሁም ሌሎች የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። በተለይም ላለፉት 17 ዓመታት ደርቆ የነበረው የሐረማያ ሃይቅ በተደረገለት የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች ወደነበረበት እንዲመለስና የውሃው መጠንም ከዓመት ዓመት እንዲጨምር ማስቻሉን ለአብነት ጠቅሰዋል። በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ በተከናወኑ ስራዎች የአርሶ አደሩንና የወጣቶችን የልማት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እየተቻለ መሆኑንም ገልጸዋል። በሐረማያ ሐይቅ ወጣቶች ተደራጅተው በዓሳ ማስገር እና በመዝናኛ ስራዎች ላይ ተሰማርተው ገቢ ማግኘት መቻላቸውን ጠቁመው፤ ዩኒቨርሲቲውም ለዚህ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የከርሰ ምድር ውሃን ከማጎልበት አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የተናገሩት ደግሞ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ተቋም መምህርና የውሃ ሃብት መሃንዲስ በቀለ ግርማ ናቸው። ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ የሚገኘውና በቅርቡ የተመለሰው የሐረማያ ሐይቅ ለዚህ የበቃው የዩኒቨርሲቲውና የአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም አርሶ አደሩ በዙሪያው ላይ በሚገኙ ተፋሰሶች ላይ ባከናወነው የተለያዩ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች መሆኑን አንስተዋል። በተለይም በአሁኑ ወቅት መስኖን በመጠቀም ለሚከናወኑ ምርትና ምርታማነት የማሳደግ ስራዎች በአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ የሚከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ለአርሶ አደሩ ጠቀሜታን እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን በማጠናከር ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ላይ የተጀመሩ ስራዎች መጠናከር እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል። የ2017 ዓ.ም ሀገራዊ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ንቅናቄ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ትናንት በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
26ኛውን የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት የአፍሪካ አህጉራዊ ጉባኤን ኢትዮጵያ ታዘጋጃለች - ግብርና ሚኒስቴር  
Jan 15, 2025 60
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 26ኛውን የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት የአፍሪካ አህጉራዊ ጉባኤ ልታስተናግድ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት ጉባኤ በየዓመቱ በግንቦት ወር በፈረንሳይ ፓሪስ የሚካሄድ ሲሆን በየሁለት ዓመቱ ደግሞ በየአህጉራቱ እንደሚካሄድ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በአፍሪካ ደረጃ 25ኛው ጉባኤ እአአ በ2023 ቦትስዋና ያስተናገደች ሲሆን 26ኛውን ጉባኤ ኢትዮጵያ እንድታዘጋጅ መመረጧንም አስታውቋል። ጉባኤው "የእንስሳት ጤና ለምግብና ስነ-ምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ለሕብረተሰብ ጤና" በሚል መሪ ሀሳብ ከጥር 27 እስከ 30/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡ ለጉባኤው መሳካት ከዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት ዋናው ጽህፈት ቤት፣ የአፍሪካ እና የምስራቅ አፍሪካ ተወካዮች ጋር የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶች ሲደረጉ መቆየታቸውም ተገልጿል። የግብርና ሚኒስቴርም ግብረ-ሃይል በማቋቋም ቅድመ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡ በጉባኤው ከየአፍካ ሀገራት የጤና ኃላፊዎችና ቋሚ ተወካዮች፣ ከዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት፣ በየአህጉሩ ያሉ የእንስሳት ጤና አመራሮች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍና የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች እንደሚታደሙም ተጠቁሟል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) በጉባኤው በአፍሪካ የእንስሳት ጤና አገልግሎት፣ ድንበር ዘለል የእንስሳት በሽታዎችን መቆጣጠርና መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ብሎም ከበሽታ ነጻ የሆነ አህጉር ለመፍጠር የሚረዱ ውይይቶች ይደረጋሉ ብለዋል። በጉባኤው በእንስሳት ጤናና ልማት፣ በምግብና ስነ-ምግብ ዙሪያ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንደሚገኙና የተለያዩ ውሳኔዎች እንደሚተላለፉበት ገልጸዋል። በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እየተሰሩ ያሉ እንደ ዝርያ ማሻሻል፣ መኖ፣ የእንስሳት ጤና እና የሕብረተሰብ ጤና አጠባበቅ በስፋት ውይይት ይደረግባቸዋል፤ አቅጣጫዎች ይቀመጡበታል ሲሉም ተናግረዋል። የእንስሳት ጤና በንጥረ ነገር የበለጸገ ምግብ ለማምረት እንደሚረዳ፣ መቀንጨርን ከመከላከል አንጻር የእንስሳት ጤና ምን ያህል አስተዋጽኦ እንዳለውም የምናይበት መድረክ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራትና በአህጉር ደረጃ ካሉ ሀገራት ጋር ድንበር ዘለል የእንስሳት በሽታዎችን ለመቆጣጠር፣ የገበያ ተደራሽነትን ለማስፋት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋልም ብለዋል። ሀገራት ያላቸውን የእንስሳት በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ስትራቴጂና ተሞክሮ፣ ኢትዮጵያም በእንስሳት ጤና፣ መሰረተ ልማት እና ያሉ መልካም አጋጣሚዎችን ለዓለም የምታስተዋውቅበት፣ ልምድ የምንጋራበት መድረክ ነው ሲሉም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል። ከመቶ ዓመት የዘለለ የእንስሳት ጤና አገልግሎትና የምርምር ተቋማት፣ በእንስሳት ጤና ላይ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ፣ ክትባትና መድሃኒት የሚያመርቱ፣ በእንስሳት ጤና የሰው ሃይል የሚያፈሩ ተቋማት መኖራቸው መልካም አጋጣሚዎች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የሚካሄደው የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት የአፍሪካ ጉባኤ የእንስሳት ጤና እንዲጠበቅ ብሎም ዘርፉ እንዲነቃቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ማለታቸውም በመረጃው ተመላክቷል።
የአሜሪካ 39ኛ ፕሬዝዳንት ጂሚ ካርተር በ100 ዓመታቸው አረፉ
Dec 30, 2024 181
አዲስ አበባ፤ ታኅሳስ 21/2017 (ኢዜአ)፡- የአሜሪካ 39ኛው ፕሬዝዳንት የነበሩት ጂሚ ካርተር በ100 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የቀድሞ ፕሬዝዳንቱ በመጨረሻው ጊዜያቸው በፔሊንስ ጆርጂያ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው “በቤተሰቦቻቸው ተከበው ነበር” ሲል ካርተር ሴንተር በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ካርተርን “ውድ ጓደኛ” እና “ልዩ መሪ” ሲሉ የተሰማቸውን ሀዘን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው አሜሪካውያን ለቀድሞው ፕሬዝዳንት “የምስጋና እዳ አለባቸው” ብለዋል። የአሜሪካ መንግሥት የቀድሞ ፕሬዝዳንቱን ሥርዓተ ቀብር ለመፈጸም ዝግጅት እያደረገ ስለመሆኑ የሲ.ኤን.ኤን ዘገባ አመልክቷል። የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጂሚ ካርተር ባለቤት ሮዛሊን ካርተር እ.ኤ.አ. በ2023 ወርሃ ኅዳር በ96 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ሁለቱ ጥንዶች ለ75 ዓመታት አብረው በትዳር አብረው ኖረዋል። ካርተር እ.ኤ.አ. ከ1977 እስከ 1981 አሜሪካን በፕሬዝዳንትነት መርተዋል። ፕሬዝዳንት ካርተር እ.ኤ.አ. በ1980 በተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የካሊፎርኒያ ገዢ በነበሩት ሮናልድ ሬገን ሲሸነፉ የካርተር ማእከልን እ.ኤ.አ. በ1982 አቋቁመው ወደ በጎ አድራጎት ተግባር ተሰማርተው ነበር። የካርተር ማእከልም ከኢትዮጵያ ጋር በሽታን በከላከልና በመቆጣጠር፣ የምግብ ምርትን በማሳደግ፣ ግጭትን በማስወገድና በምርጫ ታዛቢነት በመሳተፍ የረጅም ጊዜ ግንኙነት ነበረው።
ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ተሸፍኗል- ሚኒስቴሩ
Dec 24, 2024 224
ደሴ፤ ታኅሣሥ 15/2017 (ኢዜአ)፦ በአገር አቀፍ ደረጃ ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መሸፈኑን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን(ዶ/ር)ን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ተጀምሯል። ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት የበጋ መስኖ ስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ምርት በስፋት ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው፡፡ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም ለበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው፤ በዘንድሮው የበጋ ወራት ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በላይ በስንዴ ለማልማት እየተሰራ ይገኛል፡፡ እስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴም ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር የሚበልጥ መሬት በስንዴ ዘር መሸፈን እንደተቻለ ነው የተናገሩት። ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ግብዓቶችን በበቂ መጠን እያቀረበ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአማራ ክልል ገጠር ልማት ዘርፍ አስተባባሪና ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በዚህም 254 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ በማልማት ከ9 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልፀዋል፡፡ እስካሁን ከ120 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በዘር መሸፈኑን ጠቁመዋል። በክልሉ በተሻሻለ አሰራር ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ በቂ ምርት ለገበያ እንዲቀርብ ጭምር እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ሐተታዎች
የዲፕሎማሲ ስኬት ከአዲስ አበባ እስከ አንካራ
Dec 31, 2024 227
ኢትዮጵያና ሶማሊያ በአንካራ ያደረጉት ስምምነት በአፍሪካ ቀንድ የሰላም እና የልማት ትብብርን ለማጠናከር እንደማሳያ ይወሰዳል፡፡ ምንም እንኳን ከራሳቸው የግል ስውርና የገሀድ ፍላጎት መነሻነት የሁለቱን ሀገራት ስምምነት ሊያጣጥሉ የሚሞክሩ አንዳንድ የውጭ ሀይሎች ቢኖሩም የአንካራው ስምምነት ከሁለቱ ሀገራት ፍላጎትና ጥቅም የተሻገረ ቀጣናዊ ትሩፋት ያለው ነው። የአንካራው ስምምነት ይዘቶች፣ ለሁለቱ ሀገራት እና ለቀጣናው የሚኖረው በረከት እና የስምምነቱን ተፈጻሚነት የማይፈልጉ ሃይሎች አካሄድ ምን እንደሚመስል እንዲሁም ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም፣ ልማትና ትብብር ላይ እስካሁን ያደረገችውን አበርክቶ ለመቃኘት እንሞክር። ኢትዮጵያ በአፍሪቃ ቀንድ ቀጣና የአፍሪካ ቀንድ ከ170 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርበት ቀጣና ነው። ቀንዱ ከቀይ ባሕርና ሕንድ ውቅያኖስ የሚያገናኘውን የዓለማችን ስትራቴጂካዊ ስፍራ በመያዙ ለዓለም የስበት ማዕከል ሆኗል። ቀጣናው ፖለቲካዊና ምጣኔ ሀብታዊ ጠቀሜታው ጉልህ ነው። በቀይ ባህር በየዓመቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ መርከቦች እንደሚተላለፉበት መረጃዎች ያመላክታሉ። የዓለምን 12 በመቶ የወደብ ገበያ ይሸፍናል። በዚህም ምክንያት ብሄራዊ ጥቅማቸውን ለማሳካት የሚሹ የሩቅም የቅርብም ጠላትና ወዳጅ ሀገራት አካባቢውን ለመቃኘት የሚያባክኑት ሽርፍራፊ ሰከንድ የለም። ሁሌም በአካባቢው የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን አይናቸውን ሳይነቅሉም ክትትል የሚያደርጉበት ቀጣና ነው። ቀጣናው የሃያላን ቀጥተኛና ኢ-ቀጥተኛ ዕጆች የሚበዙበት በመሆኑም ቀጣናውን ኢ-ተገማችና ተለዋዋጭ መልክ እንዲይዝ አድርጎታል። ይህ ደገሞ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ልማትና ትብብር ዋጋ እየከፈለች ላለችው ኢትዮጵያ ፈተና መደቀኑ ዕሙን ነው። ኢትዮጵያም ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር፣ ሰላምና ትብብር በየዘመኑ ከፍተኛ ዋጋ ስትከፍል ቆይታለች። ለአብነትም በመሰረተ ልማት ረገድ በድንበር ተሻጋሪ የባቡር፣ የመንገድ እና የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማት በማስተሳሰር በኩል የኢትዮጵያ ሚና ከማንም የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካም ሆነ በዓለም ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ በመሳተፍ ለሰላም እና ለነጻነት መከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ለአፍሪካ ብሎም ለዓለም ሰላምና ደህንነት መከበር የላቀ ውለታ ውላለች። በተለይም በምስራቅ አፍሪካ ለጎረቤት ሀገራት ሠላም መጠበቅ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍላለች። ሶማሊያ፣ ሱዳንና ደቡብ ሱዳን ለዚህ አብነት የሚሆኑ ሀገራት ናቸው። ለሀገራቱ ሰላም መከበር በከፈለችው ዋጋም ሀገራቱ ከግጭት ቀውስ እንዲወጡ፣ መንግሥታቱ በሁለት እግራቸው እንዲቆሙ አድርጋለች። ሶማሊያ አጣብቂኝ ውስጥ በገባችበት ወቅት ሁሉ ኢትዮጵያ በሚቀብላት ጥያቄ መሰረት አልሻባብን በመዋጋት ህዝቡን ከዕልቂት ሀገሪቱንመ ከመበታተን ታድጋለች። ኢትዮጵያ ለሀገራት ሰላምና ደህንነት ለተጫወተችው ሚናም ዓለም አቀፍ ዕውቅና ተችሯታል። ዛሬም ለቀጣናው ሠላም፣ የጋራ ልማትና ትብብር ሌት ተቀን እየሠራች ትገኛለች። በቅርቡ ከሶማሊያ ጋር የተደረሰው የአንካራው ስምምነት ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ያላትን የጸና አቋምና ቁርጠኝነት ያሳየችበት የዲፕሎማሲ ድል ነዉ። የአንካራው ስምምነት-የዲፕሎማሲ ስኬት ማሳያ በያዘነው ታኅሣሥ ወር መባቻ ላይ በቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን አሸማጋይነት የተደረገው የአንካራ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት የቀረፈ ስምምነት ነው። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ሰላምና ትብብርን የሚያጎለብት፣ የሀገራቱን ሕዝቦች ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር፣ ለቀጣናው ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና የሚበጅ ሲሉ በርካቶች ታሪካዊ ስምምነት እንደሆነ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት፣ የአውሮፓ ሕብረትና ኢጋድ አድንቀውታል። እንግሊዝ፣ ጀርመንና አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስምምነቱ ለቀጣናው ያለውን ፋይዳ በማውሳት አሞካሽተውታል። በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ ሀገሪቱን ወደቀይ ባህር የመለሰ ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ድል ተሰኝቷል። በቀጣናው ሰላም የከፈለችውን ዋጋም ዕውቅና ያሰጠ ነው። የአንካራ ስምምነት ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታገኝ ለምታደርገው ጥረት በር ከፋች ሆኗል። በዚህም የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት መሻት ዓለም አቀፍ ዕውቅና እንዲያገኝ አስችሏል። በዚህም የኢትዮጵያ የወደብ ጥያቄ ህጋዊ ሞራላዊ እና ፖለቲካዊ መሰረት ያለው ነው። ይህም ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ የዘርፉ ምሁራንም ስምምነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር ለወዳጅ ሀገራት ጭምር ተስፋ የፈነጠቀ ክስተት ነው፡፡ ስምምነቱ ለአደራዳሪዋ ቱርኪዬ ጭምር የዲፕሎማሲ ተቀባይነቷን ያሳደገ ነው። ቱርኪዬ በአፍሪካ ቀንድ ለምታደርገው ተሳትፎ መሸጋገሪያ ድልድይ እንደሚሆናት ተንታኞች ይናገራሉ። በጥቅሉ ስምምነቱ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው በመጥቀስ ኢትዮጵያ ሚዛን የሚደፋ ድል እንድትቀዳጅ አስችሏታል ይላሉ። የፀረ-አንካራ ስምምነት ሃይሎች ስምምነቱ ቀጣናውን ለማተራመስ ስውር ዓላማ ሰንቀዉ ለሚንቀሳቀሱ አካላት ራስ ምታት ሆኗል። ዓለም በአንድ ድምጽ ያደነቀውን፣ የቀጣናውን ሠላም በማስጠበቅ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የዓለም ሀገራት እና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች እየመሰከሩለት ያለውን ይህን ስምምነት ከአላስፈላጊ ጣልቃ ገብነት ለመጠበቅ የሁሉንም ርብርብ ይፈልጋል፡፡ ስምምነቱ የቀጣናውን ሰላም እና መረጋጋት የማይሹ አካላት እኩይ አላማ ያከሸፈ ነዉ፡፡ ሆኖም እነዚህ አካላት በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስምምነቱ ግቡን እንዳይመታ መጣራቸው የማይቀር ነው፡፡ የሁለቱ ሀገራት ስምምነት እንዳይሰምርም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሶማሊያ ላይ በሚያሳድሩት አሉታዊ ጫና ዋና እና ተጎጂ ሶማሊያ እና የሶማሊያ ህዝብ መሆናቸው የእነዚሁ አካላት የቀደሙ ጣልቃ ገብነቶች ያስከተሉት ጉዳት ጥሩ ማሳያዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሃይሎች ለሶማሊያውያን አንድነት እና ሰላም ከፍተኛ ዋጋ የከፈለውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በማጥላላት በየሚዲያዎቻቸው የሚያናፍሱት መሰረተ ቢስ መረጃ በሁለቱ ሀገራት ስምምነት እኩይ አላማቸው ላይሳካ በአጭር መቀጨቱን የሚያሳይ ነው:: የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ ከሶማሊያ ጋር ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደሚያጤኑት መግለፃቸው በአሸዋ መሰረት ላይ የገነቡት ሴራ መፍረሱን የሚያመላክት ሆኖም ታይቷል፡፡ እነዚህ አካላት ሶማሊያ በከፋ የውስጥ ችግር ውስጥ በነበረችበት ወቅት አይተው እንዳላየ ሲያልፉ ቢቆዩም የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ግን ለሶማሊያ መጠናከር እና የውስጥ ሰላም መስፈን የሚያደርጉት ድጋፍ ጊዜ እንደማይሽረው እና ጥቅም እንደማይለውጠው በተግባር የታየ ሀቅ ነው፡፡ የአንካራው ስምምነትም በደምና በመስዋዕትነት የተሳሰረው የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ወንድማማችነት ቢቀጥንም የማይበጠስ መሆኑን አመላካች ነው ላይበጠስም ተቋጥሯል።
ፊሽካዬ ማስተናገጃዬ፤ ሞባይሌ ግብር መክፈያዬ ነው- ሕይወትን ማቅለል የሚወዱት እማማ ፊሽካ!
Dec 25, 2024 190
እኒህ እናት የዘመነ ኑሮ፤ ቀለል ያለ ኑባሬ ይወዳሉ። በርግጥ የተጸውዖ ስማችው ቤዛዊት ኃይለስላሴ ይሰኛል። ብዙሃኑ ከተሜው ግን በ'እማማ ፊሽካ'ነት ያውቃቸዋል። በአዲስ አባበ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰሜን ማዘጋጃ አካባቢ ጠበብ ያለችው ምግብ ቤት ባለቤት ናቸው- እማማ ፊሽካ። ገበያቸው የደራ ነው። ገበያቸውን ያደራው፤ እርሳቸውን ያሳወቃቸው ደግሞ አንድም ፊሽካቸው ነው፤ አንድም የምግባቸው አቀራረብና ስያሜ ነው። የምግብ ዋጋቸውም ቢሆን ተመጣጣኝ ነው። ወደ እማማ ፊሽካ ቤት ጎራ ያለ ደንበኛ ሁሉ ዕጁን በቅጡ መታጠብ ግድ ይለዋል። ሳይታጠብ ወደ ማዕድ የሚቀርብ ደንበኛ ካስተዋሉ እማማ ፊሽካ እንደ ትራፊክ ፊሽካቸውን ያስጮሃሉ። ይህ ልዩ ክዋኔያቸው ደግሞ ዝናቸውን አስናኝቷል። ቤታቸውን አሳውቋቸዋል። ደንበኞችም፤ ሚዲያውም ወደ ወደ ደጃቸው እንዲደርስ ዕድል ፈጥሮላቸዋል። በደንበኞቻቸው ዘንድም ከበሬታን አትርፎላቸዋል። እማማ ፊሽካ ሰኔ 14 ቀንን አይረሱትም። ለእርሳቸው ልዩ ቀን ነው። ለምን ቢሉ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ እማማ ፊሽካ ቤት ጎራ ብለው ማዕዳቸውን ተቋደሰው ነበርና- 'ዶክተር ዐቢይ' የተሰኘውን ምግብ። እማማ ፊሽካ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በድንገት ወደ ምግብ ቤታቸው መከሰታቸውን አስመልክቶ "በሕይወቴ ደንግጬ የማላውቀውን አይነት ድንጋጤ ነው የተሰማኝ" ብለው ነበር በወቅቱ። እናም የዕድሜ ባለጸጋዋ ወይዘሮ ቤዛዊት ከንጋት እስከ ምሽት ፊሽካቸውን እንደ ሜዳሊያ አንገታቸው ላይ አንጠልጥለው ምግብ ቤታቸውን ይቆጣጠራሉ። የእማማ ፊሽካ ታማኝነትና ከበሬታም ከቤታቸው የተሻገረ ነው። ለሙያቸው ብቻ ሳይሆን ለግብራቸውም ታምነዋል። ግብራቸውን በወቅቱና በታማኝነት ይከፍላሉ። ግብር መክፈል የተሻለች ሀገር ለመገንባት የሚያግዝ 'የሀገር አደራ፣የውዴታ ግዴታ' እንደሆነ ያምናሉ። ለዚህም ወደ ገቢዎች ቢሮ በጊዜ ያመራሉ። ዳሩ በግብር አከፋፈል ስርዓቱ ለእማማ ፊሽካ መሰል ግብር ከፋዮች ቀላልና ምቹ አልነበረም። ወደ ግብር መክፈያ ቦታዎች መመላለሱና ወረፋ መጠበቁ ከስራ ባህሪያቸው ጋር አብሮ አልሄድ እያላቸው ሲቸገሩ ቆይተዋል። ዛሬ ግን ይህን እንግልት የሚቀርፍ ፈጣንና ምቹ የግብር አከፋፈል ስርዓት መዘርጋቱን ወይዘሮ ቤዛዊት ይናገራሉ። ድሮ 'ሲስተም የለም' እየተባሉ የሚጉላሉት አሰራር አሁን በቀላሉ ስራ ቦታቸው ሆነው ግብራችውን መክፈል እንዲችሉ አስችሏቸዋል። ቀለል ያለ የኑሮ ዘይቤ ለሚሹ ለእርሳቸው አይነት ሰዎች ይህ ወደር የሌለው ደስታ ፈጥሮላቸዋል። የዲጂታል ግብር መክፈያ ቴክኖሎጂው ለዕድሜ ባለጸጋዋ እማማ ፊሽካ በፊሽካቸው ደንበኞቻቸውን እንዲያስተናግዱ፤ በሞባይላቸው ደግሞ ግብራቸውን እንዲከፍሉ አስቸሏቸዋል። "ፊሽካዬ ማስተናገጃዬ፤ ሞባይሌ ደግሞ ግብር መክፈያዬ" የሚሉት እማማ ፊሽካ፤ ሕይወት ቀለል እንዳለላቸው ይግልጻሉ። በርግጥ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አከፋፈል ስርዓት ለንግዱ ማህበረሰብ በጅቷል። እንደ እማማ ፊሽካ ሁሉ አቶ ደጉ ሃብቴ እና አቶ መላኩ መና፤ የዘመነ ግብር አከፋፈል ሕይወትን ቀለል እንዳደረገላችው ይናገራሉ። የዲጂታል ቴክኖሎጂው ባሉበት ሆነው በቀላሉ መክፈል በማስቻሉ የጊዜ ብክነትንም፣ እንግልትንም ቀንሶላቸዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰውነት አየለ፤ በመዲናዋ ለሁሉም ግብር ከፋዮች የሚመች የዲጅታል አሰራር ስርዓት እንደተዘረጋ ይናገራሉ። የዘመነ እና ቀልጣፋ ግብር አከፋፈል ስርዓቱን ለመተግበር የደረጃ " ሀ እና ለ " ግብር ከፋዮች "ኢ-ፐይመንት እና ኢ- ፋይናንስ" በተሰኙ ዲጂታል አማራጮች በቀላሉ ግብራቸውን እንዲከፍሉ ማስቻሉን ይገልጻሉ። ይህ ደግሞ ደንበኞች ጊዜን፣ ገንዘብን እና ጉልበትን በቆጠበ መልኩ ያለምንም እንግልት ግብራቸውን እንዲከፍሉ እንደሚያግዝ ገልጸው፤ ደንበኞች ይህን አማራጭ በመቀጠም ግዴታቸውን ይወጡ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።          
የማንሰራራት ዘመን አብነት የሆነው የማዕድን ዘርፍ እመርታ
Dec 20, 2024 3518
ኢትዮጵያ ተፈጥሮ ሁሉን አድሏታል። መሬቷ የሰጡትን አብቃይ ነው። አብቃይ ብቻ ሳይሆን ገፀ ምድሯና ከርሰ ምድሯም በማዕድን የበለጸገ ነው። የውሃ ሀብቷ የቀጣናው ‘ውሃ ማማ’ ያሰኛታል። የብዝዝሃሕይወቷ፣ የአየር ንብረቷና በእንስሳት ሀብቷም ‘ሁሉ በደጄ’ ያሰኛታል። በዓለም ላይ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጧም ስትራቴጂካዊ ስፍራ ያደርግታል። የሕዝብ ብዛቷም ሌላው ዕምቅ አቅም ነው። ይህ ሁሉ ተፈጥሯዊ ዕምቅ ጸጋዋ ወደ ብልጽግና ማማ ከፍታ ይወስዳታል። ጸጋዋን በቅጡ ለይታ ከተጠቀመች ከራሷ አልፎ ለሌሎችም ትተርፋለች። የዜጎቿን ማህበራዊ ፍላጎቶችንም ትመልሳለች። ባለፉት ዓመታት ያልታየ ጸጋዋን በማየት ሁሉን አቀፍ የሆነ መዋቅራዊ ኢኮኖሚያዊ ሽግግር ለማረጋገጥ ሁሉን አቀፍ ጥረት ተጀምሯል። እስካሁን እምብዛም ትኩረት ያላገኙ ዘርፎች ተለይተው ወደ ልማት ተገብቷል። በዚህም የማንሰራራት ዘመን ማሳያ የሆኑ ተጨማሪ ዘርፎች አሉ። ከነዚህም መካከል የማዕድን ዘርፉ ይጠቀሳል። ይህ ጽሁፍ የማዕድን ዘርፉን ለማንሰራራት ዘመን ያለውን አብነታዊ ጉዞ ይቃኛል። በማዕድን ግብይት አዋጅ 1144/2011 እንደተተረጎመው ማዕድን ማናቸውም ዋጋ ያለው በጠጣር፣ በፈሳሽ ወይም በጋዝ መልክ በተፈጥሮ በመሬት ላይ ወይም ውስጥ፣ በውሃ ውስጥ ወይም ስር የሚገኝ በጂኦሎጂ ሂደት ወይም ሁኔታዎች የተፈጠረ ቁስ ነው። ማዕድን በአገልግሎቱ፣ በዋጋው እና በሌሎች መስፈርቶች በብዙ መልኩ ይገለጻል። ለምሳሌ የከበረ ማዕድን፣ በከፊል የከበረ ማዕድን፣ ብረት ነክ ማዕድን፣ የኢንዱስትሪ ማዕድን እና የግንባታ ማዕድን ተብሎ። ኢትዮጵያ ተዝቆ በማያልቅ ማዕድን ከብራለች። ወርቅ፣ አልማዝ፣ የተፈጥሮ ጋዝ፣ ኤመራልድ፣ ብረት፣ መዳብ፣ ኳርተዝ፣ የድንጋይ ከሰል፣ ፓታሽ፣ ጂፕሰም፣ ላይምስቶን፣ እብነ በረድ፣ ባዛልት፣ ሳፈየር፣ ታንታለም፣ አሸዋ እና የሸክላ አፈር… ሌላም ሌላም። ዳሩ ይህ ጸጋ በቅጡ ለይታ እንዳልተጠቀመች ዕሙን ነው:: ከማዕድን ጸጋዎች ትሩፋት የመቋደስ ጅማሮ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ገቢራዊ መሆን የጀመረው የሀገር በቀል ማክሮ ኢኮኖሚ ረፎርም አምስት ምጣኔ ሀብታዊ ምሰሶዎች ለይቷል። ከነዚህ መካከል አንዱ ማዕድን ነው። በመንግስት የ10 ዓመት መሪ ልማት ዕቅድም የማዕድን ዘርፉ በሚገባ ተቃኝቷል። ለዘርፉ እመርታ አስቻይ የሆኑ ፖሊሲዎችና ሕግ ማዕቀፎች ወጥተዋል። በተለይም የተሻለ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር እና የግል በማዕድን ልማት ዘርፍ ተሳትፎው እንዲያድግ ምቹ ዕድል ተፈጥሯል። የመንግስት መሰረተ ልማት ግንባታ እና ሌሎች ቁልፍ እርምጃዎች ለግሉ ዘርፍ መተማመን ፈጥሯል። እንደ ሀገር የማዕድን ሀብቶችን በመለየት ለሀገር ልማት ወሳኝ ድርሻ በሚኖራቸው አግባብ እንዲለሙ የሚጠቁሙ ጥናቶች ቀጥለዋል። ተስፋ ሰጭ የጥናት ግኝቶችም አሉ። ለአብነትም ኢትዮጵያ የኮፐር፣ ኒኬል፣ ኮባልት፣ ሊቲየም እንዲሁም ሌሎች ውድ እና ለኃይል አማራጭ የሚውሉ የማዕድን ሀብቶች እንዳሏት በጥናት ተረጋግጧል። ለኮንስትራክሽን የሚውሉ እንደ ዕብነበረድ፣ ግራናይት፣ ላይምስቶን ፣ ባዛልት፣ አሸዋ፣ ጠጠር፣ ኢግኒምብራይትና የሸክላ አፈር፤ ለኢንዱስትሪ የሚውሉ እንደ ካኦሊን፣ቤንቶናይት፣ ኳርትዝ፣ የድንጋይ ከሰል፣ ላይምስቶን፣ ፖታሽ እና ግራፋይት እንዲሁም ለብረታ ብረት ዘርፉ የሚውሉ እንደ ኒኬል፣ ማንጋኒስ፣ ነሃስ እና እርሳስን ጨምሮ ሌሎችም ማዕድናት አሏት። ጸጋዋን ለማልማት ደግሞ ከማስተዋወቅ ይጀምራል። የማዕድን ሚኒስቴር በዘመኑ ቴክኖሎጂ የታገዘ የማዕድን ጋለሪ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት አድርጓል። ለአልሚዎችም ለተመራማሪዎችም ምቹ የግንዛቤ ሁኔታ ይፈጥራል። በየዓመቱም የውጭና የሀገር ውስጥ የዘርፉ ኩባንያዎችን ያሳተፈ የማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ እየተደረገ ነው። ሕገ ወጥ ግብይትን ለማስቆም የሚያስችል ስራም ተጀምሯል። የማክሮ ኢኮኖሚው የተሟላ ሪፎር ትግበራ ደግሞ ዘርፉን ከማስተዋወቅ ወደ ልማት እንዲገባ ሌላ ዕድል አምጥቷል። ዘርፉን የማስተዋወቅ፣ መረጃዎችን የማደራጀት፣ ምቹ የኢንቨስትመንት ሕግ ማዕቀፍ እና ማበረታቻ ስርዓቶች ተዘርግተዋል። በ10 ዓመት መሪ ዕቅዱ የማዕድን ዘርፍ በየዓመቱ 33 በመቶ ዕድገት እንዲኖረው ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም የማዕድን እና ቴክኖሎጂ(ማይንቴክስ) ኤክስፖ ላይ ለዘርፉ ልማት የተሰጠው ትኩረት ከውጭ ገቢ ማዕድን ግብዓትን መተካት ብቻ ሳይሆን ወደ ውጪ በመላክም የሀገርን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ገልጸው ነበር። ማዕድን ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግና ለምታደርገው ጉዞ መሰረት የሚሆን ወሳኝ ዘርፍ መሆኑንም እንዲሁ። የማዕድን ዘርፍ የእስካሁን እመርታና አበርክቶ በ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ከዘርፍ 17 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ግብ ተቀምጧል። በተለይም የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ኢኮኖሚውን እንዲደግፍ ታልሟል። ማዕድን ሚኒስቴር እ.አ.አ በ2023 ባወጣው መረጃ 170 የአገር ውስጥ እና ውየጭ ኩባንያዎች በወርቅ፣ ነዳጅ፣ ብረት፣ ጂኦ ተርማል እና መሰል የማዕድን ሀብቶች ፍለጋ እና ልማት ላይ ተሰማርተዋል። በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ስራ ዕድል ፈጥሯል። በ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት ወደ ውጭ ከተላኩ ማዕድናት 420 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል። በተያዘው በጀት ዓመት ደግሞ 800 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ይጠበቃል። በሩብ ዓመቱም ከግማሽ ቢሊዮን ዶላርበላይ ገቢ ተገኝቷል። ከማዕዳናት መካከል የወርቅ ማዕድን የውጭ ምንዛሬ አንቀሳቃሽ ሞተር ቢባል ማጋነን አይሆንም። ወርቅ የ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት የማዕድን ዘርፍ ወጪ ንግድ ገቢ 70 ከመቶውን ይሸፍናል። በተያዘው ዓመት የመጀመሪያ ሶስት ወራትም 561 ሚሊዮን ዶላሩ አስገኝቷል። ይህን አቅም ይበልጥ ለማሳደግ ዘመናዊ አመራር መከተል፣ የወርቅ ግብይት ሕጋዊነት እና የምርት ጥራት ማረጋገጥ እና የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ማሳደግ ላይ ተተኩሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጋምቤላ ክልል የሚገኘውን “ኢትኖ ማይኒንግ” የወርቅ ማምረቻ ፋብሪካ በቅርቡ መመረቃቸው ይታወቃል። የፋብሪካው መገንባት የወርቅ አንቨስትመንት በአጭር ጊዜ ያሳየውን አመርቂ ውጤትና ደረጃውን የጠበቀ የወርቅ ምርት ከማስገኘቱ ባሻገር ሕገ ወጥ ለሆነ የማዕድን ስራም ምላሽ የሚሰጥ እንደሆነ ገልጸዋል። በዘንድሮው በጀት ዓመት ከወርቅ ወጪ ንግድ 2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት መታቀዱን በመጠቆምም፤ በቀጣይ ኩባንያው የወርቅ ምርትን በዕጥፍ ለማሳደግ ተጨማሪ አቅም እንደሆነ ጠቅሰዋል። ቀጣይስ? መንግስት ከወርቅ ማዕድን በተጨማሪ በኦፓል፣ ድንጋይ ከሰል እና ሌሎች ማዕድናት የወጪ ንግድ ገቢ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከሰሞኑ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ የብረት ኢንዱስትሪ መንደር የሚገኘውን ስቲሊ አር. ኤም. አይ ኃላ/የተ/የግ/ የብረታ ብረት ማምረቻ ፋብሪካ መጎብኘታቸው ይታወቃል። መንግስት የማዕድን ዘርፍ በማልማት ከዘርፉ ሀገራዊ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ እንደሆነ በወቅቱ ገልጸዋል። የጎበኙት የብረታ ብረት ፋብሪካም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት የሚኖረውን ቁልፍ ሚና ጠቅሰዋል። መንግስት ለዘርፉ ፈተና የሆኑ እንደ ጸጥታ ችግር፣ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ እና የአሰራር ማነቆዎች ለመፍታት ለዘርፉ እመርታ በትኩረት እንደሚሰራበትም አረጋግጠዋል። በጥቅሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት ዘመን አብነት ሆኗል። የእስካሁን ጅማሮው ተስፋ ሰጪነት በቀጣይ የማዕድን ዘርፉ የኢትዮጵያ በረከት እንደሚሆንና ብልጽግናዋን ለማረጋገጥ ትልቅ አቅም እንደሚሆን እርግጥ ነው።
ፍሪልዮን - ለሀገር ለወገን የሚሰጥ ተመን አልባ ስጦታ
Dec 20, 2024 190
ግራና ቀኝ እያማትርኩና ውስጤ የሚመላለሰውን ብዙ ሀሳብ መልክ እያስያዝኩ (በስዊዘርላንድ ዳቮስ ከተማ ወደ ሚገኝ አንድ የኤግዚቢሽን አዳራሽ) ሳዘግም ድንገት ቀልቤን የሚይዝ ጽሁፍ ከባሻገር ተመለከቱ። 'A Frillion Dollar worth Idea' ይላል ጽሁፉ። ፍሪሊዮን የሚባል ቁጥር መኖሩን ከዚያ ቀደም ሰምቼ ስለማላውቅ፣ ይህ ደግሞ ስንት ነው? በሚል ጉጉት ወደ ኤግዚቢሽኑ ጎጆ ቀረብ አልኩኝ። . . . ከሩቅ 'ፍሪልዮን' ብዬ ባነበብኩት ሰሌዳ ላይ ያለው ጽሑፍ ቀረብ ብዬ ሳየው 'የትሪሊዮን ዶላር ሀሳብ' ነበር የሚለው። በማላውቀው ምክንያት ለወትሮው የሰማይ ጥግ ሆኖ የሚታየኝ ትሪሊዮን ከማውቃቸው ትንንሽ ቁጥሮች አንዱ ሆኖ ታየኝ። ፍሪልዮን ከሚባለው ቁጥር አንጻር ሁሉም ቁጥሮች ደቃቅ እና ድንክዬ ሆነው ታዩኝ። ፍሪልዮን የቁጥሮች ንጉስ ሆኖ ታየኝ፤ ቁጥሮች ሁሉ ቁጥራቸውን የሚያገኙበት የቁጥሮች ምንጭና ልኬት። ከሰሌዳው ላይ የተገለጸውን የትሪሊዮን ዶላር ሃሳብ ምንነት እንኳን በቅጡ ሳላጣራ ውስጤን ካነቃው የፍሪልዮን ሀሳብ ጋር እየተጫወትኩ ወዲያ ወዲህ ማለቴን ቀጠልኩ። ከሚሊዮን ጀምሮ ያሉ ትልልቅ ቁጥሮች የጋራ መለያቸው እና ድንበራቸው '-llion'/'-ሊዮን' የሚለው ድህረ ቅጥያ ሲሆን ትክክለኛ ትርጉሙ ይህ ነው ለማለት ባይቻልም የግዙፍ ቁጥሮች መለያ ሆኖ ያገለግላል። በእርግጥ መጨረሻው ላይ 'ዮን' የሚለው ድምጸት በጣሊያንኛ የብዛት አመልካች ቅጽል ነው። ከትሪሊዮን ወደ ዜሮ ከዚያም ተመልሼ ወደ ፍሪልዮን ስመጣ ብዙ ጥያቄዎች በፍጥነት ወደ አእምሮዬ እንደ ጅረት ሲፈስሱ ቆዩ። ይህ ሁሉ የሆነው በአጭር ጊዜ ውስጥ ነበር። ሀሳብና ምናብ ከጊዜ ውጭ የሚሰሩ የሌላ አለም ክፋዮች ሳይሆኑ የቀሩም። "Free" ነፃ፣ "llion" ደግሞ ደግሞ የቁጥር ታርጋ። "ፍሪልዮን" ነጻ ቁጥር፤ ነፃን የሚያክል ቁጥር ወሰን የሌለው ነጻ ቁጥር፤ ለሀገር፣ ለወገን፣ ለፈጣሪ የሚሰጥ ተመን አልባ ስጦታ። የፍሪልዮን ዶላር ኢንቨስትመንት፣ በነጻ በመስጠት መክበር። መስጠት - መስጠት - መስጠት። መስጠት ደማቅ አሻራን አትሞ የማለፍ ትልቅ ምስጢር ነው። በነጻ መስጠት ደግሞ የፍሪልዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ነው። ለዘመናት በገዳ ስርዓት ራሱን ሲያስተዳድር የኖረው የቦረና አርብቶ አደር በነጻ መስጠትን በተመለከተ አንድ አስደናቂ ልማድ አለው። የቦረና አካባቢ ቆላማ በመሆኑ ክረምት ከበጋ የሚፈሱ ወንዞችና ምንጮች እምብዛም የሉትም። ከብቶቹን እና ግመሎቹን ውሃ ለማጠጣት ኤላ ተብሎ የሚታወቅ ጉድጓድ ቆፍሮ ማዘጋጀት ግድ ይለዋል። ኤላ አጠገብ ለእንስሳት የውሃ መጠጫ ገንዳ ይኖራል። የቦረና አርብቶ አደር ውሀውን ከኤላ አውጥቶ እንስሳቱን አጠጥቶ ዝም ብሎ አይሄድም። እንስሳቱን አጠጥቶ እንደጨረሰ ገንዳውን በውሀ ሞልቶ መሄድ ለዘመናት የቆየ ልማዱ ነው። እንስሳቱ ጠጥተው ከጨረሱ በኋላ ገንዳውን ውሃ ሞልቶ የሚሄዱ ምስጢር ሌላ አይደለም። ውሃ የተጠሙ የዱር እንስሳት እና አእዋፍ በውሀ ጥም እንዳይቸገሩ ውሃን ለዱር ፍጥረታት በነፃ የመስጠት ባህል ነው። ትልልቆቹ የሰው ልጅ በረከቶች በዋጋ የሚታመኑ አይደሉም። ፍቅር፣ ውበት፣ እውነት፣ እምነት፣ ምስጋና፣ . . . በገንዘብ የምናገኛቸው ነገሮች አይደሉም። ማንም በገንዘብ ድሃ የሆነ ሰው እነዚህን መስጠት ይችላል። ተፈጥሮ እነዚህን ሀብቶች ለሁሉም ሰው የሰጠችው ሁሉም ሰው እነዚህን ኢንቨስት አድርጎ በረከት እንዲሰበስብ ነው። ሰላምታንና ፈገግታን እንውሰድ። አንድ ሰው ሰላምና ፈገግታ በመስጠት ብቻ የዓለምን ቋጥኞች መናድ ይችላል። ለመስጠት እስከፈለግን ድረስ የምንሰጠው አናጣም። እኛም በነፃ የተሰጠን አለና። ሁሌም መስጠታችንን ለማብዛት እንሞክር። አለም ለማይሰጠጥ ሰው ክብር የላትም። ያለውን ካልሰጠ የሰጠችውን ትነጥቀዋለች። መስጠት በሌለበት መቀበል ከየት ይመጣል? ከይቅርታ ውጪ ፍቅር፣ ከሰላም ውጭ ደስታ ይኖራል ብለን ማሰብ አንችልም። እርግጥ ነው ዛሬም ቢሆን መግደል ማሸነፍ፣ መጣል መብለጥ በሚመስላቸው አዕምሮዎች ውስጥ መስጠትና ማካፈል፣ ፍቅርና ይቅርታ፣ መጨመርና መሙላት ሳይሆን መቀነስና መጉደል ተደርጎ ይቆጠራል። መስጠት ዞሮና በዝቶ የሚመለስ ብድር ሳይሆን፣ ላይታፈስ ፈስሶ እንደቀረ ውሀ፣ ተቃጥሎ አመድ እንደሆነ ማገዶ ይታሰባል። . . . . . . መብራቱን፣ ስልኩን፣ ራዲዮውን፣ ቴሌቪዥኑን፣ መኪናውን ወዘተ የሰጠን ሌላ ሰው ነው። ያለሰው ብቻችንን አንድ ቀን እንኳን መዋል አንችልም። በምድር ላይ ሰው ሁሉ ጠፍቶ ብቻችንን ብንቀር ምን የምንሆን ይመስለናል? እንደ አዲስ ድንጋይና ድንጋይ አፋጭተን እሳት እንለኩስ ካልሆነ በስተቀር አሁን ያሉን በረከቶች ሁሉ አይኖሩንም። ድንጋይ ከማፋጨት የገላገለን አብሮነት ነው፤ መስጠትና መቀበል ነው። ምሉዕ ሰው መሆን የሚቻለው በመደመር ብቻ ነው። ለብቻ ሰው መሆን የለም። ግለሰብ ሆኖ የቀረ በሞት ይቀጫል፤ ያበቃለታል። "ግለሰብ" ቤተሰብ ከዚያም ህብረተሰብ፣ ማህበረሰብና ሀገረሰብ እያለ ሲበዛ ሞት የማያቆመው ችግር የማይረታው የሰውነት ምስጢር ይገለጣል፤ ምሉዕ ህይወት በፍሪልዮን ብቻ ትለካለች። ምንጭ:- የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመደመር መንገድ መጽሀፍ (ገጽ 327 - 339)
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 451
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 715
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 919
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 2278
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 644
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 2072
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
   ያ ሆዴ የአዲስ ብርሃን ተስፋ
Sep 21, 2024 3921
በማሙሽ ጋረደው ከሆሳዕና የኢዜአ ቅርንጫፍ ከብት የሚጠብቁ ህፃናት አዲስ ዓመት እየመጣ ስለመሆኑ ማብሰሪያ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ የዋሽንት /የገምባቡያ/ ድምፅ ማሰማት ይጀምራሉ። በመስከረም ከጉምና ጭጋግ ፀለምት ጨለማ የሚወጣበትና ምድሩ በአበባ ሀምራዊ ቀለም የሚታጀብበት ወቅት በመሆኑ በሀዲያ ብሄር ዘንድ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ወቅት ነው። ያ ሆዴ የሀዲያዎች አዲስ የዘመን መለወጫ በዓል መባቻ ነው። ያ ሆዴ ማለት በሀዲያዎች ዘንድ “ብርሃን ሆነ፣ መስቀል መጣ፣ ገበያው ደራ፣ በይፋ ተበሰረ ብሎም እንኳን ደስ አላችሁ” የሚል ስያሜ እንዳለውም ይነገራል። “ያ ሆዴ " በሀዲያ ካሉ እሴቶችና ወጎች እንዲሁም ክንዋኔዎች መካከል አንዱ ሲሆን፤ አንድነት፣ መቻቻል፣ ለውጥን ለማሳለጥ፣ አብሮነትና ሰላም ለማጠናከርም ከፍተኛ ሚና እንዳለው ይወሳል። የሀዲያ አገር ሽማግሌ አቶ መንገሻ ሂቤቦ እንዳጫወቱን ከሆነ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ ከብት የሚጠብቁ ህፃናት አዲስ ዓመት መምጣቱን የዋሽንት /የገምባቡያ/ ድምፅ በማሰማት አዋጅ ማብሰር ይጀምራሉ። ይህም የበዓሉ መቅረብን ለማሳሰብና ለማስታወቅ የሚደረግ ነው። በዓሉ ብርሃን፣ብሩህ ተስፋ፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ረድኤት በረከት የሚሞላበት ተምሳሌታዊ ወር ተደርጎ ይታመናል። ያ ሆዴ በሀዲያ ዘንድ ልዩ ስፍራ የሚሰጠው በዓል ነው። በዓሉ ከመድረሱ በፊት ሁሉም የቤተሰብ አባላት በዓሉን ለማድመቅ የየራሳቸው ድርሻ አላቸው። ለምሳሌ አባት ለእርድ የሚሆን ከብት በማቅረብ፣ እናት ደግሞ ሌሎች የቤት ስራዎች በማከናወንና ልጆችም ልዩ ልዩ የስራ ድርሻቸውን በመወጣት በዓሉን ያከብራሉ። “አባቶች አብሮነታቸውን ከሚያጠናክሩባቸው ማህበራዊ እሴቶች መካከል አንዱ ቱታ /ሼማታ/ ነው” ይላሉ የሀዲያ አገር ሽማግሌ አቶ መንገሻ፤ ይህም ከአራት አስከ ስምንት አባላትን ይዞ የሚደራጅ የስጋ ማህበር ነው። የማህበሩ አባላት ግንኙነት ያላቸው የሚተሳሰቡ የኢኮኖሚ አቅማቸውም ተቀራራቢነት ያለው ሲሆን፤ በዓሉ ከመድረሱ በፊት በጋራ ገንዘብ ማስቀመጥ ይጀምራሉ። ለስጋ መብያ የሚሆን ቆጮ ብሎም ለአተካና የሚሆን ቡላ በማዘጋጀት ከጥቅምት እሰከ ጥር ባሉት ወራት ውስጥ እንሰት በመፋቅ እናቶች በቡድን ተሰባስበው ዝግጅታቸውን ማከናወን ይጀምራሉ። በተጨማሪም ዊጆ |የቅቤ እቁብ| በመግባት ቅቤ በማጠራቀም ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑ ቅመማ ቅመሞችን በማዘጋጀት ኃላፊነታቸውን ይወጣሉ። የዳጣ፣ የአዋዜ ዝርያዎችንና ለበዓሉ ማድመቂያ የሚሆኑ ባህላዊ የሆኑ መጠጦችን ጭምር ያዘጋጃሉ። ልጃገረዶች በዓሉ እንዲደምቅ ቤት መደልደል፣ የተለያዩ ቀለማትን በመጠቀም የግርግዳ ቅርጻ ቅርጾችን በመስራት እንዲሁም ግቢ በማጽዳት የማሳመር ስራቸውን ያከናውናሉ። ወጣት ወንዶች ለማገዶ የሚያገለግል በአባቶች ተለይቶ የተሰጣቸውን እንጨት ፈልጠው እንዲደርቅ ያደርጋሉ። ጦምቦራ ለደመራ የሚሆን ችቦ በማዘጋጀት ግዴታቸውን ይወጣሉ። የሀዲያ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ባለሙያ ወይዘሮ አመለወርቅ ሃንዳሞ እንደሚሉት፤ በዓሉን ለማክበር በአገር ውስጥ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆች ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ አብሮነት ለማክበር ከእሩቅም ከቅርብም ይሰበሰባሉ። ይህም በዓሉ ለአብሮነትና ለሰላም ያለውን ፋይዳ የላቀ ያደርገዋል። ዓመቱን ሙሉ ለበዓሉ የሚደረጉ ዝግጅቶችና የስራ ክፍፍሎች ልዩ ትርጉም ያላቸው ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ “ወጣቶች የትዳር አጋራቸውን የሚመርጡበት በመሆኑ በዓሉን ልዩ ድባብ ይሰጠዋል” ይላሉ ወዘሮ አመለወርቅ። የበዓሉ ዋዜማ /ፉሊት ሂሞ/ ወጣቶች ያዘጋጁትን ጦምቦራ /የደመራ ችቦ/ የአካባቢውን ነዋሪዎች በሚያዋስን ቦታ ላይ ይሰራሉ። እናቶች ከቡላ፣ ቅቤና ወተት የሚያዘጋጁት ጣፋጭ የሆነ እና ጣት የሚያስቆረጥመውን አተካና በማዘጋጀት የበዓሉን ዋዜማ/ፉሊት ሂሞን/ ያደምቁታል። የበዓሉ አመሻሽ ዋዜማ ላይ ወጣቶች “ያ ሆዴ ያ ሆዴ “በማለት ይጨፍራሉ። ይህም ለበዓሉ “የእንኳን አደረሳችሁ” መልእክት አለው። በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የአገር በቀል እውቀቶች ምርምር ዳይሬክተር አቶ እያሱ ጥላሁን “ይህ በዓል የሚሰጠው የስራ ክፍፍል፣ የሰላምና አብሮነት ዕሴቶች ለጠንካራ ዕድገት፣ ነገን በተስፋ ለመመልከት ወሳኝ ነው” በማለት ይገልጹታል። በወቅቱ ወጣቶች በአካባቢው እየዞሩ በመጫወት ከአባቶች ምርቃት ይቀበላሉ። የአካባቢው ነዋሪዎች ደመራው በተዘጋጀበት ቦታ ማምሻውን ይሰባሰቡና አባቶች ደመራውን የሚያቀጣጥሉበትን ችቦ በመያዝ ልጆችን በማስከተል ዓመቱ የብርሃን፣ የሰላም፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እንዲሆን ፈጣሪያቸውን በመማጸን ደመራውን ይለኩሳሉ። ደመራው ተቀጣጥሎ እንዳለቀ በእድሜ ከፍ ወዳሉ አባወራ ቤት እንደሚሰባሰቡ ነው አቶ እያሱ የተናገሩት። የእርድ ስርዓቱ በሚከናወንበት ቤት ደጃፍ አባላቱ ቤተሰቦቻቸውን በመያዝ በአንድነት በመሰባሰብ የጋቢማ ስርዓት ይከናወናል። ይህም እድሜ ጠገብ ሽማግሌዎች ቅቤ እና ወተት በሚታረደው በሬ ላይ እያፈሰሱ” ለምለም ሳር "በመያዝ በሬውን እያሻሹ አዲሱ ዓመት ለህዝብ እና መንግስት የሰላም ዓመት የሚመኙበት መንገድ ነው። ልጆች ለወግ ለማዕረግ የሚበቁበት፣ መካኖች የሚወልዱበት፣ የተዘራው ለፍሬ የሚበቃበት ዓመት እንዲህን ፈጣሪያቸውን ይማፀናሉ። በሦስተኛው ቀን የቱታው አባላትና የአካባቢ ሰዎች ተጠርተው በአባቶች ምርቃት ተደርጎ በአንድነት ሆነው ምክክር በማድረግ ለቀጣይ ዓመት የሚሆን እቅድ በማዘጋጀት ተጨዋውተው ይለያያሉ። “በየቤቱ የሄደው ቅርጫ በፍጹም ለብቻ አይበላም” ያሉት አቶ እያሱ፤ በየአከባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችን አፈላልጎ ማብላትና ማጠጣት በማከናወን በዓሉን በጋራ ያሳልፋሉ። ይህም በዓሉ አንዱ ለአንዱ ያለውን ወዳጅነትና አብሮነትን በማጠናከር ትስስርን የማጉላት አቅሙ ከፍተኛ ነው። በሌላ በኩል ተጣልቶ የከረሙ ነዋሪዎች ከተገኙ በሰከነ መንፈስ በመነጋገር እርቀ ሰላም በማውረድ በንጹህ ህሊና፣ በአዲስ ምዕራፍ፣ በአዲስ ተስፋና በአዲስ መንፈስ አዲሱን ዓመት ይጀምራሉ። ይህም “ባህሉ በዜጎች መካከል የሰላምና አብሮነት ምሰሶ መሆኑን ያመለክታል” ያሉት አቶ እያሱ፤ በንጹህ ልቦና በብርሃንና በተስፋ መጪውን ዘመን ለማሳለፍ እንዲቻል ጉልህ ሚና እንዳለው አጽንኦት ይሰጡታል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 44139
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 37357
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 26328
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 23665
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 21940
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 20358
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 19923
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 19541
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 44139
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 37357
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 26328
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 23665
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ወንዞቿን ከብክለት ወደ ትሩፋት ለመለወጥ የተነሳችው አዲስ አበባ
Jan 13, 2025 127
  አዲስ አበባ ከተቆረቆራች አንድ ከግማሽ ምዕተ ዓመት ልትደፍን ጥቂት ዓመታት ይቀራታል። ከተማዋ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ዑደት አስኳል ሆና ሁሉን አስተናግዳለች።   ዕድል ቀንቷት ከኢትዮጵያዊያን አልፋ የአፍሪካዊያን መዲና ሆናለች። ዘመን ችሯት የዓለም ዲፕሎማሲ ማዕከል አድርጓታል። ከአፍሪካ ወደ ዓለም፤ ከዓለም ወደ አፍሪካ መግቢያና መውጫ በር ናት። የሀገሪቷ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ዕድገት የስበት ማዕከል ናት። በፍጥነት ያደገችና ነዋሪቿን ያበዛች፤ ምጣኔ ሀብትን ያጎለመሰች ከተማ ናት። ዳሩ የከተሜነት መዋቅራዊ ፕላኗ አኳያ ውስንነቶች እንደሚስተዋልባት በባለሙያዎች ዘንድ ይነሳል። ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ዘመን ተሻጋሪ፣ ለኑሮ ምቹና ስሟን የሚመጥን የክትመት ዕቅድ ይዛ ባለመጓዟ ውበትም፤ ኑረትም፣ ምቾትም አጉድላለች። በጽዳትና ውበቷ ረገድ በእንግዶቿም ዘንድም ለትቸት ተጋልጣ ታውቃለች። ከአዲስ አበባ ድክመቶች አንዱ የብዙ ወንዞች ባለቤት ሆኗ አንዱንም እሴት ጨምራ ወደ ሀብትትነት አለመቀየሯ ነው። ፈሳሽ ወንዟን አልምታ በውበት አለመፍሰሷ። በመዲናዋ ከ76 ያላነሱ ዋና እና ገባር ወንዞች ይገኛሉ። ዳሩ በየዘመኑ የከተማ ልማት ዕቅዶች የወንዝ ዳርቻን ታሳቢ ባለማድረጋቸው ወንዞቿ ለገጽታዋ ውበት ሳይሆን ሳንካ ሆነዋታል። የከተሜነት ወጓ ከወንዞቿ ልማት ጋር አልተመራም። የሰዎች አሰፋፈር ከዓለም አቀፋዊ የከተሜነት ልክን አልጠበቀም። ይህ ደግሞ ወንዞች ለነዋሪዎቿ ጠንቅ እንጂ ትሩፋት እንዳይሆኑ አድርጓል። በርካታ ሀገራት ከተሞች ጥቂት ወንዞቻቸውን ለጌጥም፤ ለበረከትም አውለዋል። ባለበዙ ወንዞች ባለቤቷ አዲስ አበባ ግን "ጽድቁ ከርቶ..." እንዲሉ ከወንዞቿ ጥቅሟ ቀርቶ፤ ጠንቋ በዝቶ ቆይታለች። ወንዞቹን ለምተው ለዘርፈ ብዙ አገልግሎት ከመዋል ይልቅ ለብክለት ተጋልጠው ለሕዝብ ጤና ጠንቅ ነበሩ። በክረምት ወራትም ጎርፍ እየተሞሉ ነዋሪዎችን ለአደጋ አጋልጠዋል። እነሆ አሁን የዘመናት ክፍተቷን ለመቅረፍ ተነስታለች። ከተማ አቀፍ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ተጀምረዋል። የመዲናዋን ወንዞች ከሕዝብ ጤና ጠንቅነት ወደ ጥቅም የመለወጥ ተግባር እየተከናወነ ይገኛል። በአዲስ አበባ ከሚፈሱ ወንዞች መካከል እስካሁን አንድ ወንዝ ለቱሪስት መስህብነት፣ ለመዝናኛነትና ለሌላ አገልግሎት ለማዋል የተሰራ የተፋሰስ ልማት እየተከናወነ ነው። የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የበርካታ ሀገራት ከተሞች የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ወንዞችን አልምተው ለቱሪስት መነሃሪያ እንዲሆኑ በማስቻል ለቱሪዝም ዘርፍ እመርታ ወሳኝ ድርሻ እንዲይዙ ማድረጋቸውን ይጠቅሳሉ። አዲስ አበባ ግን በርካታ ወንዞችን ታቅፋ ይህን መልካም ዕድል አልምታ ሳትጠቅም በመቆየቷ ቁጭት የሚፈጥር ጉዳይ እንደሆነ ያነሳሉ። እናም እየተከናወነ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት የህብረተሰቡን አኗኗር ብቻ ሳይሆን ለተፋሰስ ልማትም ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ወንዞች ከጠንቅነት ወደ ህዝብ ጥቅምነት የመለወጥ ስራዎች እንደቀጠሉ ከንቲባዋ አብስረዋል። በዚህም አዲስ አበባ ካሏት 76 ወንዞች መካከል አንድ ሶስተኛው ትልልቅ ወንዞቿ ለቱሪስት መዝናኛ አገልግሎት መዋል የሚችሉ ናቸው ብለዋል። ከነዚህም መካከል እስካሁን ሁለት ወንዞችን በወንዝ ዳርቻ ልማት በማስገባት ወደ ዘርፈ ብዙ ጥቅም የመለወጥ ጉዞ መጀመሩን ተናግረዋል። በትናንትናው ዕለት የከተማዋ አመራሮች እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማቶችን ጎብኝተው ነበር። ከተጎበኙ የከተማ ልማት ስራዎች መካከል የቀበና ቁጥር-1 እና 2 እንዲሁም ከእንጦጦ-ፍሬንድ ሽፕ- ፒኮክ የወንዝ ዳርቻ ልማት ይገኝበታል። ከንቲባዋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የወንዝ ዳርቻ ልማት ከብክለት ነጻ አካባቢን በመፍጠር፣ ከተማዋን ጽዱና አረንጓዴ በማድረግና በሽታን በመከላከል ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል። የእንጦጦ-ፍሬንድ ሽፕ- ፒኮክ የወንዝ ዳርቻ ልማት የተለያዩ ፓርኮችን በማስተሳሰር በፕላን የተገነባ ከተማን እውን ማድረግ የሚያስችል እንደሆነ በማብራራት። በቀበና ቁጥር 2 እንዲሁም ከእንጦጦ- ፍሬንድ ሽፕ- ፒኮክ የወንዝ ዳርቻ አፍንጮ በር አካባቢ የመጓተት ችግሮችን በመቅረፍ ስራው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። 70 ደረጃ እና 40 ደረጃ ታሪካዊ ቅርስነታቸውን ጠብቀው እየታደሱ እንደሚገኙ ገልጸው፤ ከዕይታ ተደብቆ የቆየውን የራስ መኮንን ሀውልት ከቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ዕድሳት ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ፒያሳ አካባቢ እየተሰራ የሚገኘው የወንዝ ዳርቻ ልማት አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የሩጫ፣ የሳይክል፣ የመዋኛና ሌሎች ቦታዎችን ነው። ልማቶቹ አለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችንና ሁነቶችን ለማስተናገድ የሚያስችሉ እንደሆኑ ከንቲባዋ በጉብኝቱ ወቅት አብራርተዋል። የህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሾች፣ ፓርኪንግ፣ የታክሲ ተርሚናል፣ ሱቆችንና ሌሎች ልማቶችን አካቶ እየተሰራም ነው። ፕላኑን የጠበቀ ዘመናዊ ከተማን እውን የሚያደርግ ከንቲባዋ ጠቁመዋል። የወንዝ ዳርቻን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አቀፍ የልማት ስራዎች ዘመናዊ ከተማን ያሟሉ በመሆኑ ለአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ይጨምራሉ።
    የምግብ ሉዓላዊነት፤ ከተረጂነት እና ጠባቂነት መላቀቂያ መንገድ
Jan 10, 2025 195
ኢትዮጵያ ራሷን ከተረጂነት ለማላቀቅ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራች ትገኛለች። የዜጎችን የምግብ ፍላጎት በራስ የምርት አቅም የመሙላት ስራ በማከወን ከውጭ አገራት ምርት ጠባቂነት ለመላቀቅ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ከልመና ወጥታ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ውጭ ገበያ መላክ መጀመሯ ትልቅ ታሪካዊ ድል ነው። ከውጭ የኢኮኖሚ ጥገኝነት በመላቀቅ የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት ለማስከበር በስንዴ ልማት የተመዘገበውን ስኬት በሌሎች የግብርና መስኮች ለመድገም በመሰራት ላይ ይገኛል። በሩዝ፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ሻይ ቅጠልና ሌሎች የተለያዩ ሰብሎች ላይ እየተከናወነ ያለው ስራ ተጨባጭ ውጤቶች እያስገኘ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምግብ ዋስትናና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ የአመራር ቁርጠኝነት ከዓለም የምግብ እና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) የአግሪኮላ ሜዳልያ በጥር ወር 2016 ዓ.ም ያበረከተው ሽልማት ለምግብ ሉዓላዊነት ጥረት የተሰጠ እውቅና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የኢትዮጵያ መንግስት ረሃብን ሙሉ በሙሉ ከማስቀረት ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ብሔራዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ እየሰራ መሆኑን በሽልማቱ ወቅት ገልጸው ነበር። ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሃብቶች፣ ተስማሚ የአየር ንብረትና ለስራ ትጉ የሆነ ወጣት እንዳላት እና እነዚህን ሃብቶች ታሳቢ በማድረግ የታሪክ አውራ የሆነችውን ሀገር ልማት ወደፊት ለማራመድ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ እንደከፈልን ሁሉ ከምግብ ጥገኝነት ለመላቀቅ በትጋት መስራት እንደሚገባ ተናግረው ነበር። የምግብ ሉዓላዊነት፣ የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት፣ የበጀት ሉዓላዊነት፣ ታላቁን የሀገር ሉዓላዊነት በጽናት የሚያቆሙ ናቸው። እነዚህን የሉዓላዊነት ዘርፎች ለማስከበር አዲሱ ዓይነት አርበኝነት ያስፈልገናል። ይህም የብሔራዊነት አርበኝነት መሆኑንም ከዚህ ቀደም መናገራቸው ይታወቃል። የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በዓድዋ ጦርነት ያስመዘገበችውን አኩሪ ድል በዘመናዊ ግብርና የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት በማረጋገጥ እንደግመዋለን ሲሉ ገልጸው ነበር። በዓድዋ የዘመኑ ጀግኖች የሀገራቸውን የግዛት ሉዓላዊነት እንዳስከበሩት ሁሉ፣ የዚህ ዘመን ትውልድ ደግሞ ሌላ የራሱን ታሪክ መጻፍ እንዳለበት አንስተዋል። በዚህ ዘመን ደግሞ የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ድሉን ለመድገም ትልቅ ተጋድሎ እያደረገች ነው ብለዋል። ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ያሏትን ጸጋዎች እና ሀብቶች አሟጦ በመጠቀም ከተረጂነት ተላቆ ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። ከነዚህ ስራዎች መካከል አንዱ ከረድኤት ተቋማት ከሚደረግ የሰብዓዊ ድጋፍ ተላቆ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተደረገ ያለው ጥረት ይገኝበታል። የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የሀገርን ክብርና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ በራስ አቅም የሰብዓዊ ድጋፍን መሸፈን ይገባል በሚል እሳቤ አዲስ ስትራቴጂ ነደፎ እየሰራ ይገኛል። ይህ በስራ ላይ የዋለው ፖሊሲ የሀገርን ሉዓላዊ ነፃነት እና የዜጎችን ክብር በማስጠበቅ አደጋን በራስ አቅም ምላሽ በመስጠት የክምችትና የመጠባበቂያ ፈንድ አቅምን ማጎልበት የሚያስችል መሆኑን አስታወቋል። ለዚህም ሀገር አቀፍ የስትራቴጂክ መጠባበቂያ ክምችት አቅም ከ23 በመቶ ወደ 47 በመቶ የሚያሳድጉ ዘመናዊ የክምችት መጋዘኖች እየተገነቡ መሆኑን የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል። ይህም የመፈጸም አቅምን በማሳደግ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን በሚል ስኬታማ የአሰራር ማሻሻያ ሥርዓት መዘርጋቱን የሚያሳይ ነው። በ2016 ዓ.ም ጸድቆ ወደ ስራ የገባው የአደጋ ስጋት አመራር ፖሊሲ ዋነኛ ማጠንጠኛው በራስ አቅም የሰብዓዊ እርዳታን መሸፈን ላይ ያተኮረ ነው። የክልሎች ራስን የመቻል ስራዎች ፖሊሲው የውጭ እርዳታን ብቻ ሳይሆን ክልሎች ከፌደራል መንግስት ድጋፍ ተላቀው ራሳቸውን እንዲችሉ የማድረግ አቅም መገንባት ላይ መስራት እንደሚያስፈልግ የሚያመላክት ነው። በዚሁ መሰረት ድሬዳዋና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ ስድስት ክልሎች የሰብዓዊ ድጋፍ ጥያቄዎችን በራሳቸው መሸፈን የሚያስችል አቅም መፍጠራቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል። በቀጣይም ሁሉም ክልሎች ራሳቸውን እንዲችሉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጿል። በኦሮሚያ ክልል ለመጠባበቂያ እህል ክምችት የሚውል ከ43 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በመኸርና በበጋ ወራት እርሻ በማልማት 1 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን የቡሳ ጎኖፋ ኦሮሚያ መረጃ ያመለክታል። በክልሉ ከማኅበረሰቡ የቆየ የመረዳዳት እሴት ተቀድቶ በክልሉ "ቡሳ ጎኖፋ ኦሮሚያ" በሚል ስያሜ በተቋም ደረጃ ተቋቁሞና ሕጋዊ እውቅና አግኝቶ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየሰራ ይገኛል። እየተከናወነ የሚገኘው የእርሻ ሥራ ክልሉ አሁን ላይ ያለውን 100 ሺህ ኩንታል የመጠባበቂያ እህል ክምችት ወደ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል የሚያሳድግ መሆኑንም ተመላክቷል። በክልሉ የምርት ማከማቻ መጋዘኖችን በሕዝብ ተሳትፎ በክልሉ በሚገኙ 21 ዞኖችና በተመረጡ ስምንት ከተሞች ላይ ለመገንባት የዝግጅት ሥራዎች ተጠናቀው ወደ ስራ ተገብቷል። በአማራ ክልል ከተረጅነት ለመላቀቅና እርዳታን በራስ አቅም ለመሸፈን በ36 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ለመጠባበቂያ እህል ክምችት የሚውል ሰብል ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል። በክልሉ በ2016/17 ምርት ዘመን ልማቱን በ36 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ለማካሄድ ታቅዶ እስካሁን ከ27 ሺህ 700 ሄክታር የሚበልጥ መሬት በመለየት ወደ ተግባር መግባቱን ቢሮው ገልጿል። ለምርት ማሳደጊያ የሚውል 1 ሺህ 914 ኩንታል ማዳበሪያና 1 ሺህ 154 ኩንታል ምርጥ ዘር ቀርቦ ጥቅም ላይ እየዋለ እንደሚገኝም እንዲሁ። በራስ አቅም የመጠባበቂያ እህል በማምረት ዕርዳታን ሳይጠበቅ ለችግር ለሚጋለጡ ዜጎች ተደራሽ በማድረግ ክልሉን ከተረጅነት ለማላቀቅ የተያዘው ግብ እንዲሳካ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ቢሮው አመልክቷል። ሌላኛው የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ የመሸፈን አቅም ጥረት ማሳያ የሲዳማ ክልል ነው። በክልሉ ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ የሚሆን የምግብ ሰብል ክምችት በወል መሬት የማልማት ስራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተጠቁማለ። በዚህም በክልሉ በመኸር እርሻ 800 ሄክታር የወል መሬት ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ እንዲሆኑ በተለያዩ ሰብሎች መልመካቱን መረጃዎች ያመለክታሉ። የሲዳማ ክልል የተረጂነት ጉዳይ የሉአላዊነት ጉዳይ መሆኑን ከግምት በማስገባት በራስ አቅም የመጠባበቂያ ምግብ ክምችት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሰብአዊ እርዳታን በራስ አቅም ለመሸፈን የክልሉ መንግስት የተለያዩ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በራሱ እያለማ ያለው የሰብል ማሳ የዚሁ ስራ ማሳያ ነው። ኮሚሽኑ በዘንድሮው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ በ56 ሄክታር ማሳ ላይ በቆሎ፣ ማሽላ፣ አኩሪ አተር እና ሌሎች ሰብሎችን እያለማ እንደሚገኝ ገልጿል። በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች በምግብ ራስን መቻል እና ሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን በሚል መርህ የተለያዩ ሰብሎች እየለሙ መሆኑንም አመልክቷል። ሌላኛው በተሞክሮነት የሚጠቀስ ስራ እያከናወነ የሚገኘው ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ነው። ክልሉ ለድንገተኛ የተፈጥሮ አደጋ በራስ አቅም ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም ለመገንባት ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። እምቅ የልማት አቅምን በመጠቀምና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን መቻል የክልሉ መንግስት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎታል።   በዚህም በቀጣይ ሁለት ዓመታት በክልሉ የሴፍቲኔት መርህግብር ተጠቃሚዎችን ወደ ዘላቂ ልማት በማሸጋገር ከተረጂነት የሚወጡበት ልዩ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል። አረንጓዴ አሻራ እና የሌማት ትሩፋትን በማስተሳሰር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በክልሉ ከተረጂነት ወጥቶ ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ጥረት ማሳያ ናቸው። ሌሎች ክልሎችም በራሳቸው አቅም የሰብዓዊ ድጋፍ ለመሸፈን በመስራት ላይ ይገኛሉ። ተግባራቱ ከተረጅነት ለመላቀቅና እርዳታን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተደረገ ያለውን የባህል ለውጥ በግልጽ የሚያሳዩ ናቸው። የመውጫ ሀሳብ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ እርዳታ የሚሹ ወገኖችን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል አሁናዊ በቂ የሰብዓዊ ድጋፍ ክምችትና ዝግጅት መኖሩን የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል። መንግስት በተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ምክንያቶች የሚከሰቱ አደጋዎችን መቋቋም የሚያስችሉ ሀገራዊ ፖሊሲና ስትራቴጂ ቀርጾ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አመልክተዋል። በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች የሚከሰቱ አደጋ ስጋቶችን ለመቋቋምና ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን ለመድረስ ማህበረሰቡ እርስ በርስ የሚተጋገዝበትን ስርዓት ለማጠናከር ትኩረት መደረጉንም እንዲሁ። በሌላ በኩል የመጠባበቂያ ክምችት በመፍጠር ሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም በዘላቂነት ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል ሀገራዊ አቅም ለመፍጠር ወደ ስራ መገባቱንም ኮሚሽነሩ አንስተዋል። በዚህም ካሳለፍነው ክረምት ጀምሮ እስከ በ2017/2018 የምርት ዘመን 253 ሺህ ሄክታር መሬት በማረስ 2 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ወይም 20 ሚለዮን ኩንታል ምርት በማምረት መጠባበቂያ ክምችት ለመያዝ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። እስከ አሁንም 108 ሺህ ሄክታር መሬት መታረሱን ገልፀው፤ ይህም የዕቅዱን 43 ከመቶ ይሸፍናል ነው ያሉት። ዕቅዱን ዕውን በማድረግ እንደ ሀገር ሙሉ የመጠባበቂያ ክምችት በመያዝ በፌደራልና በክልል ደረጃ ቀዳሚ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ። በሀገር ደረጃ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት አቅም የሚፈጥሩ ናቸው። ኢትዮጵያ ከ26 ሀገራት ለመጡ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎችን አስጠልላ ከለላና የተለያዩ መሠረታዊ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ ትገኛለች። እንደ የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት መረጃ ከሆነ በስደተኞች ስም የመጣ ማንኛውም ድጋፍ ለታለመለት ዓላማመዋሉን የመከታተልና የመቆጣጠር ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ ከዋና መሥሪያ ቤት ጀምሮ የስደተኛ ማዕከላት ድረስ የክትትልና ቁጥጥር ሥርዓት ዘርግቶ እየሠራ ይገኛል። በዚህም መሠረት ሩሲያ የደቡብ ሱዳንን የእርስ በርስ ጦርነት ተከትሎ ወደ ኢትዮጵያ የገቡና በጋምቤላ ክልል ለተጠለሉ የደቡብ ሱዳን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች በዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) በኩል 1 ሺህ 632 ነጥብ 4 ሜትሪክ ቶን የስንዴ ድጋፍ ትናንት አድጋለች። የስደተኞች ሰብዓዊ ድጋፍ ከተለያዩ መንግስታትና ዓለም አቀፍ ተቋማት በሚደረግ ድጋፍ በዓለም የምግብ ፕሮግራም በኩል ሲከናወን ቆይቷል፤ የአሁኑ ድጋፍም የተደረገው ለተመሳሳይ ዓላማ እንደሆነም አገልግሎቱ አመልክቷል። ኢትዮጵያ የአጋር አካላት ድጋፍ መቀዛቀዙን ተከትሎ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የተለያዩ አገራት ስደተኞች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ በተደጋጋሚ ጊዜ ጥሪ ማቅረቧ ይታወቃል። ዓለም አቀፍ ረጂ አካላትም ስደተኞች ሰብዓዊ መብታቸው ተጠብቆ መሠረታዊ አቅርቦት እንዲያገኙ ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸውም ስትገልጽ ቆይታለች። በሀገር ደረጃ እየተደረጉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት አቅም የሚፈጥሩ ናቸው። ኮሚሽኑ የሰብዓዊ አገልግሎት፣ ዘላቂ ልማትና የሰላም ጥምረትን በማረጋገጥ ዕውቀት መር በራስ አቅም አደጋን ምላሽ የሚሰጥ ተቋም ለመገንባት የማሻሻያ እርምጃዎችን ወስዷል። የራስ አቅም ግንባታው በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በ2030 ዓ.ም ለአደጋ ስጋት የማይበገር ማህበረሰብን ለመገንባት እቅድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። ሀገራዊ ትልሙ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት የሚያሸጋግር መልካም ጅማሮ ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም