ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ ወሳኝ ድል ተቀዳጀች
Mar 27, 2026 126
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ በ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ያለው ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ከነዓን ማርክነህ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ዋልያዎቹ ብልጫ ወስደው ተጫውተዋል። የማጥቃት እንቅስቃሴያቸው ጥሩ የሚባል ነበር። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ድልድል የመግባት እድሏን አስፍታለች። የሁለቱ ሀገራት የመልስ ጨዋታ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ ስታዲየም ይካሄዳል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈ ወደ ምድብ ድልድል ማለፉን ያረጋግጣል። የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ በመጀመሪያ ጨዋታቸው ድል ቀንቷቸዋል። 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ጁን 2027 በታንዛንያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ ጣምራ አዘጋጅነት ይካሄዳል።
ለየጤና ነገር …
Mar 27, 2026 101
ስለ ሄርኒያ (ቡዓ) ምን ያህል ግንዛቤ አለዎት? ሄርኒያ ምንድን ነው? መንስዔውስ? በዚህ ጉዳይ ላይ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የሕጻናት ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ካሳሁን ግርማ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ሙያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። • ምንነት እንደ ዶክተር ካሳሁን ገለጻ፤ ሄርኒያ (ቡዓ) ማለት በሆድ ግድግዳ ላይ ባለ ክፍተት ወይም በሆድ ግድግዳ መሳሳት ምክንያት ሆድ ውስጥ ያሉ የሰውነት ክፍሎች በዋናነት አንጀት ከተፈጥሯዊ ቦታው ሲወጣ ማለት ነው። በአብዛኛው አዲስ የተወለዱ ሕጻናትን ይይዛል፤ አንዳንድ ጊዜም ቆይቶ ሊከሰት ይችላል የሚሉት ባለሙያው፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘም እስከ 6 በመቶ የሚወለዱ ወንድ ሕጻናት የሄርኒያ ሰርጀሪ እንደሚያስፈልጋቸው ጥናቶች ያመላክታሉ ብለዋል። • መንስዔ መንስዔው እንደታካሚው ዕድሜ ይወሰናል ያሉት ዶክተር ካሳሁን፤ በአጠቃላይ መንስዔዎቹ የሆድ ግድግዳ ክፍተት እና የሆድ ግድግዳ መሳሳት መሆናቸውን ያስረዳሉ። በዚህም መሠረት በአብዛኛው ሕጻናት ላይ በዋናነት በተፈጥሮ ያለውን የሆድ ግድግዳ ክፍተት በመጠቀም ዐዋቂዎች ላይ ደግሞ የሆድ ግድግዳ በሚሳሳበት ጊዜ አንጀት አፈትልኮ ከተፈጥሯዊ ቦታ ይወጣል ይላሉ። • ምልክቶች ሕጻናት እንደተወለዱ በደንብ በሕክምና ባለሙያ ሊታዩ እንደሚገባ የሚመክሩት ዶክተር ካሳሁን ከሄርኒያ ምልክቶች መካከል፤ በታችኛው የሆድ ክፍል አካባቢ ወይም የዘር ፍሬ ከረጢት የተለየ ዕብጠት መታየት፣ ዕብጠቱ አንዳንድ ጊዜ በራሱ የሚጠፋ ወይም ደግሞ በዕጅ በሚነካበት ጊዜ ወደ ውስጥ የሚገባ ሊሆን ይችላል፣ አንዳንድ ጊዜ ወጥቶ የማይመለስ (ወደ ውስጥ የማይገባ) ዓይነት ዕብጠት ሆኖ የሆድ መነፋት መከሰት እንዲሁም ሀሞት የቀላቀለ ማስመለስ የሚሉት እንደሚገኙበት አብራርተዋል። • ሕክምና ሕክምናው በዋናነት መንስዔውን ማከም መሆኑን አስገንዝበው፤ በዚህም መሠረት መንስዔው የሆድ ግድግዳ ላይ ያለ ክፍተት ወይስ የሆድ ግድግዳ መሳሳት የሚለውን መለየት የሕክምናው አካል መሆኑን አስረድተዋል። ከዚያም አንጀት እንዳይወጣ የሆድ ግድግዳ ላይ ያለውን ክፍተት ወይም የሆድ ግድግዳ መሳሳት በቀዶ ሕክምና ማካም እንደሚቻል አረጋግጠዋል። በተፈጠረው ክፍተት አንጀት የሚወጣ እና በራሱ የማይመለስ ከሆነ በተለይም በዕጅ በሚነካበት ሠዓት ወደ ሆድ ዕቃ ውስጥ (ወደ ተፈጥሯዊ ቦታው) ካልተመለሰ የአንጀት ደም ዝውውር ስለሚስተጓጎል ጋንግሪን የመሥራት፣ የተሠራጨ ኢንፌክሽን መኖር እንዲሁም እስከ ሞት ሊያደርስ ስለሚችል ለሕክምና ቅድሚያ መስጠትን መክረዋል ባለሙያው።
“ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2026” ፎረም በ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ውሎች ፊርማ ተጠናቀቀ
Mar 27, 2026 193
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አራተኛው “ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2026” ፎረም ዛሬ ተጠናቋል። በፎረሙ ላይ የተለያዩ ዋና ዋና ዘርፎችን ያካተቱና በአጠቃላይ 13 ነጥብ 1 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚገመቱ የኢንቨስትመንት ውሎች ተፈርመዋል። በፎረሙ መጨረሻ የተከናወነው የፊርማ መርሃግብር በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና እና አግሮ-ፕሮሰሲንግ፣ በኃይል፣ በማዕድንና በሌሎች ዘርፎች ትልልቅ የኢንቨስትመንት ስምምነቶችን ያካተተ ነው። የተፈረሙት ውሎች በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ያለውን የኢንቨስተሮች እምነት እንደሚያሳይ ተገልጿል። በተጨማሪም ለስራ ፈጠራ፣ ለውጭ ምንዛሬ ግኝትና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ተጠቅሷል። በተመሳሳይ በ“ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2025” ፎረም በአጠቃላይ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር የሚገመቱ የኢንቨስትመንት ውሎች መፈረማቸው የሚታወስ ሲሆን እነዚህም ፕሮጀክቶች አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ መግባታቸው ይታወቃል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ እንደ ግንባር ቀደም የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየታየች መሆኗን ያመላክታል። ፎረሙ አዳዲስ አጋርነቶችን ለመፍጠርና ቀጣይ የኢንቨስትመንት ግንኙነቶችን ለማጎልበት ጠንካራ መድረክ መሆኑን መረጋገጡን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የአባል ሃገራቱን ጥቅም ለማስከበር መትጋት ይጠበቅበታል
Mar 27, 2026 297
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የተቋቋመለትን አላማ እንዲያሳካ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ነጻነቱን ጠብቆ መጓዝ እንደሚገባው በቤልጂየም፣ ኔዘርላንድስ እና ሉክስምበርግ (ቤኔሉክስ) አገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢትዮጵያ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ገለጹ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት (ኦ ኤስ ፒ ኤስ ) የመሪዎች ጉባኤ ነገ ይጀምራል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴን ጨምሮ በርካታ የሀገራት መሪዎች በጉባኤው ላይ ይሳተፋሉ። የድርጅቱ የመሪዎች ጉባኤ ቅድመ ስብስባ ዛሬ ተካሄዷል። በስብሰባው ላይ በቤልጂየም፣ ኔዘርላንድስ እና ሉክስምበርግ (ቤኔሉክስ) አገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢትዮጵያ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ተገኝተዋል። አምባሳደር እሸቴ በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት ለአባል ሀገራቱም ሆነ ለመላው ዓለም ወሳኝ አስተዋጾኦ ማድረግ እንዲችል ራሱን በገንዘብ እና በመዋቅር ማጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል። አስቸጋሪ በሆነው የዓለም ተቀያያሪ የኢኮኖሚና ፖለቲካ ሁኔታ ውስጥ ድርጅቱ የአባል ሀገራቱ ጥቅም እንዲከበር በትጋት መስራት እንዳለበት አመልክተዋል። አምባሳደር እሸቴ በተለይ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ድርጅቱ እ.አ.አ በ1975 ከቅኝ ግዛት በኋላ የተመሰረተ እና በቅኝ ግዛት ሲጎዱ ለነበሩ የአፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት አለኝታ እንዲሆን ታስቦ የተመሰረተ መሆኑን አስታውሰው ኢትዮጵያ ለዚህ ድርጅት መጠናከር ትኩረት ሰጥታ እንደምትንቀሳቀስ አስረድተዋል። ባለፉት ጊዜያት የድርጅቱ በጀት በአውሮፓ ህብረት ድጋፍ ይሸፈን እንደነበረ ገልጸው ድርጅቱ የተቋቋመለትን አላማ እንዲያሳካ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ነጻነቱን ጠብቆ መጓዝ እንዳለበት አስገንዝበዋል። ለዚህ ደግሞ አባል ሀገራቱ የሚጠበቅባቸውን የገንዘብ መዋጮ መክፍል እንደሚገባቸው ነው ያሳሰቡት። በቅድመ ጉባኤ ስብሰባው የበርካታ ሀገራት ተወካዮች ድርጅቱ እያበረከተ ያለውን የማይተካ አስተዋጾኦ በማድነቅ የተሻለ ጠንካራ ሆኖ በሚወጣበት ጉዳይ ላይም ሀሳባቸውን ሰጥተዋል። በአባል ሀገሪቱ ያለውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ማሳደግ፣ የወጣቶችን አቅም በሚገባ መጠቀም ከዳያስፖራው ማህበረሰብ ጋር ያለን ትስስር በማሳደግ ለሁለንተናዊ እድገት መጠቀም የሚሉት በስፋት የተንሸራሸሩ ሀሳቦች ናቸው። በአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ያለውን ድህነት በማጥፋት ኢኮኖሚያዊ እድገትን ማፋጠንን አላማ በማድረግ የተመሰረተው ድርጅቱ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት አይነተኛ የትብብር ማዕከል ሆኖ እያገለገለ ነው። ከአውሮፓ ሀገራት ጋር ያለው የንግድ፣ ልማት፣ ዴሞክራሲ፣ አስተዳደር እና ሰብዓዊ ጉዳዮች ትብብር ደግሞ የደቡብ- ሰሜን ትስስርን በማጠናከር ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኢኮኖሚው ምሶሶ እንዲሆን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር አለባቸው
Mar 27, 2026 255
ሮቤ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ ሳይንስና ቴክኖሎጂ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ መሪ ሚና እንዲጫወት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ ፈጠራና ኢንተርፕረነርሺፕ ላይ አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችና ግኝቶች ላሏቸው ወጣቶች ሲሰጥ የቆየውን ተግባር ተኮር ሥልጠና በማጠናቀቅ የእውቅና መርሐ ግብር አካሄዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ሳይንስና ቴክኖሎጂ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ መሪ ሚና እንዲጫወት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር ይገባቸዋል። ሚኒስቴሩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የኢኮኖሚው ምሶሶ እንዲሆን በሀገር ደረጃ የተቀረጸውን ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አክለዋል። በተለይ ክህሎትና አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብና ግኝት ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር ፕሮጀክቶቻቸው በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጣ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽንና የፈጠራ ምህዳርን በማስፋትና በዘርፉ የዳበረ ማህበረሰብ በመፍጠር ረገድ በተከናወኑ ሥራዎች አበረታች ለውጦች መታየታቸውን አመልክተዋል። በተለይ ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያበረታታ "ስታርት አፕ አክት" የተሰኘ የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖረውና የፋይናንስ ድጋፍ በማግኘት ወደ ኢኮኖሚ እንዲቀየር እየተደረገ መሆኑን በማሳያነት አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም በሀገር አቀፍ ደረጃ ባለፉት ዓመታት በዘርፉ የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ በማጠናከር ከወቅቱ ዓለም ዓቀፋዊ ሁኔታ ጋር የተናበበና በዘርፉ እመርታዊ ለውጥ ለማምጣት ያለመ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ ከመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችና ግኝቶች ላሏቸው ወጣቶች ያዘጋጀው የእውቅና መድረክ የዚሁ ጥረት አካልና ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ዩኒቨርሲቲው በባሌ፣ በምስራቅ ባሌና በምዕራብ አርሲ ዞኖች በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቴክኖሎጂ ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች በመመልመል የክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም በዩኒቨርሲቲው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል ሥልጠና ያገኙ ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በ2017 ዓ.ም በተካሄደው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውድድር አንደኛ ደረጃን በመያዝ ሽልማትና እውቅና ማግኘታቸው የዘርፉ ትኩረት ውጤት መሆኑን ለአብነት አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብና ግኝት ያላቸው ግለሰቦች በሥራቸው ስኬታማ እንዲሆኑና ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ተግዳሮቶችን እንዲረዱ የተሰጠው የአቅም ግንባታ ሥልጠና የጥረቱ አካል መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አክለዋል። እውቅና ያገኙ የፈጠራ ባለቤት የሆኑ ወጣቶች በበኩላቸው ያገኙት ተጨማሪ ዕውቀትና እውቅና የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሳቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ፖለቲካ
የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የአባል ሃገራቱን ጥቅም ለማስከበር መትጋት ይጠበቅበታል
Mar 27, 2026 297
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የተቋቋመለትን አላማ እንዲያሳካ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ነጻነቱን ጠብቆ መጓዝ እንደሚገባው በቤልጂየም፣ ኔዘርላንድስ እና ሉክስምበርግ (ቤኔሉክስ) አገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢትዮጵያ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ገለጹ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት (ኦ ኤስ ፒ ኤስ ) የመሪዎች ጉባኤ ነገ ይጀምራል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴን ጨምሮ በርካታ የሀገራት መሪዎች በጉባኤው ላይ ይሳተፋሉ። የድርጅቱ የመሪዎች ጉባኤ ቅድመ ስብስባ ዛሬ ተካሄዷል። በስብሰባው ላይ በቤልጂየም፣ ኔዘርላንድስ እና ሉክስምበርግ (ቤኔሉክስ) አገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢትዮጵያ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ተገኝተዋል። አምባሳደር እሸቴ በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት ለአባል ሀገራቱም ሆነ ለመላው ዓለም ወሳኝ አስተዋጾኦ ማድረግ እንዲችል ራሱን በገንዘብ እና በመዋቅር ማጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል። አስቸጋሪ በሆነው የዓለም ተቀያያሪ የኢኮኖሚና ፖለቲካ ሁኔታ ውስጥ ድርጅቱ የአባል ሀገራቱ ጥቅም እንዲከበር በትጋት መስራት እንዳለበት አመልክተዋል። አምባሳደር እሸቴ በተለይ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ድርጅቱ እ.አ.አ በ1975 ከቅኝ ግዛት በኋላ የተመሰረተ እና በቅኝ ግዛት ሲጎዱ ለነበሩ የአፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት አለኝታ እንዲሆን ታስቦ የተመሰረተ መሆኑን አስታውሰው ኢትዮጵያ ለዚህ ድርጅት መጠናከር ትኩረት ሰጥታ እንደምትንቀሳቀስ አስረድተዋል። ባለፉት ጊዜያት የድርጅቱ በጀት በአውሮፓ ህብረት ድጋፍ ይሸፈን እንደነበረ ገልጸው ድርጅቱ የተቋቋመለትን አላማ እንዲያሳካ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ነጻነቱን ጠብቆ መጓዝ እንዳለበት አስገንዝበዋል። ለዚህ ደግሞ አባል ሀገራቱ የሚጠበቅባቸውን የገንዘብ መዋጮ መክፍል እንደሚገባቸው ነው ያሳሰቡት። በቅድመ ጉባኤ ስብሰባው የበርካታ ሀገራት ተወካዮች ድርጅቱ እያበረከተ ያለውን የማይተካ አስተዋጾኦ በማድነቅ የተሻለ ጠንካራ ሆኖ በሚወጣበት ጉዳይ ላይም ሀሳባቸውን ሰጥተዋል። በአባል ሀገሪቱ ያለውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ማሳደግ፣ የወጣቶችን አቅም በሚገባ መጠቀም ከዳያስፖራው ማህበረሰብ ጋር ያለን ትስስር በማሳደግ ለሁለንተናዊ እድገት መጠቀም የሚሉት በስፋት የተንሸራሸሩ ሀሳቦች ናቸው። በአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ያለውን ድህነት በማጥፋት ኢኮኖሚያዊ እድገትን ማፋጠንን አላማ በማድረግ የተመሰረተው ድርጅቱ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት አይነተኛ የትብብር ማዕከል ሆኖ እያገለገለ ነው። ከአውሮፓ ሀገራት ጋር ያለው የንግድ፣ ልማት፣ ዴሞክራሲ፣ አስተዳደር እና ሰብዓዊ ጉዳዮች ትብብር ደግሞ የደቡብ- ሰሜን ትስስርን በማጠናከር ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀው የክርክር መድረክ መራጩ ህዝብ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ድምፅ እንዲሰጥ ምቹ መደላድል ይፈጥራል
Mar 27, 2026 260
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀው ወጥ የሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ መራጩ ህዝብ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ድምፅ እንዲሰጥ ምቹ መደላድል እንደሚፈጥር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባዘጋጀው የመጀመሪያው የክርክር መድረክ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት(ሰላም)፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) ፓርቲ፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት እና ብልፅግና ፓርቲ ተሳትፈዋል። የክርክር መድረኩን አምስቱ የቦርዱ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በይፋ አስጀምረውታል። በዚሁ ወቅት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ የክርክር መድረኩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጭና ፕሮግራሞቻቸውን ነጻ፣ ገለልተኛና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለህዝብ የሚያደርሱበት ነው ብለዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን ለህዝብ የሚያደርሱበትን ወጥ የሆነ የክርክር መድረክ ለማመቻችት በርካታ የሙከራ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቀዋል። የክርክር መድረኩ መራጩ ህዝብ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚፎካከሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አማራጭ ሃሳቦች በማጤን በዕውቀትና በመረጃ ላይ የተመሰረተ ድምፅ እንዲሰጥ ማድረግ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል። በምርጫ ክርክር የዝግጅት ምዕራፉ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጫቸውን ለህዝብ የሚያደርሱባቸው ርዕሰ ጉዳዮች በገለልተኛ ሙያተኞች ጥናት መካሄዱንም አስታውሰዋል። በተጨማሪም በክሩክሩ ወቅት የሚቀርቡ አሃዛዊ መረጃዎችና ሀሳቦች ትክክለኝነት የሚመዝኑና የሚያጣሩ ባለሙያዎች እንዲካተቱ መደረጉንም አንስተዋል። በክርክር መድረኩም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች እንዲገኙ በማድረግ ለዲሞክራሲ ምኅዳር መጎልበት ከፍተኛ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አካታችነተና አሳታፊነትን ለማረጋገጥ የሚደረጉ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጩ ህዝብ በቀረቡት የማኑዋልና ዲጂታል አማራጮች ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በስፋት እየወሰደ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የክርክር መድረኩም መራጩ ህዝብ ድምፅ መስጫ ካርድ እንዲወስድ ከፍተኛ መነቃቃት እንደሚፈጥር ሰብሳቢዋ ጨምረው ገልጸዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ተዘጋጅተናል
Mar 27, 2026 244
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። በዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች አስፈላጊ የምርጫ ቅድመ ዝግጅቶችም እየተከናወኑ ይገኛሉ። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ወጣቶች እንደገለጹት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት በዝግጅት ላይ ናቸው። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወጣት መዲና መሀመድ ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎች ላይ በመሳተፍ እንደ ዜጋ ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የሚጠበቅባትን ድርሻ መወጣቷን ገልጻለች። ዘንድሮ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ ማውጣቷን ገልጻ፤ የወጣቱን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለው ብላለች። ወጣት ኤርሚያስ ወንድሙ በበኩሉ፤ በምርጫው ወጣቱን ጨምሮ የዜጎችን ተጠቃሚነት ከፍ ወዳለ ደረጃ ለማሸጋገር ለሚሰራ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅቻለሁ ሲል ገልጿል። የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚችለውን ፓርቲ ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ ወስዶ በመጠባበቅ ላይ መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት ኢሳ ሰኢድ ነው፡፡ ሌላኛዋ ወጣት የተመኝ አስማማው በበኩሏ፤ ምርጫው የዲሞክራሲ መብት ተጠቃሚነትን የምናረጋግጥበት መንገድ በመሆኑ ያስተዳድረኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብላለች፡፡ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት በረከት ቢርቢርሳ፤ ማህበሩ ከዚህ ቀደም በነበሩ ምርጫዎች ላይ ወጣቶች የተሻለ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የማስተባበር ሚናውን ሲወጣ መቆየቱን አንስቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ለወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ በመስራት በምርጫው አስተዋጿቸውን እንዲያበረክቱ እየሰራ መሆኑን ተናግሯል፡፡
ኢትዮጵያና ፈረንሳይ በሰላም ማስከበር ዘርፍ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት የሚያጠናክር ስምምነት ተፈራረሙ
Mar 27, 2026 301
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ በሰላም ማስከበር ዘርፍ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስልታዊ አጋርነት ማሳደግ ያለመ የሁለትዮሽ ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ (ኢ/ር) እና በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ላሜክ ፈርመዋል፡፡ ስምምነቱ በዋናነት በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ የሚሰማሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላትን ኦፕሬሽናል ዝግጁነት ለማሳደግና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ብቃት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው። በስምምነቱ መሰረት፣ የዓለም አቀፍ የሰላም ድጋፍ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት (IPSTI) እና የኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት (CTS) የሚሰጡ የሥልጠና ሰርተፊኬቶች ዓለም አቀፍ ዕውቅና እና የምርምር ተግባራት ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ይደረጋል። በተጨማሪም ስምምነቱ የኢትዮጵያ የሰላም ማስከበር ማዕከል የሚሰጡ የስልጠና ሰርተፊኬቶች በተባበሩት መንግሥታትና በአፍሪካ ሕብረት ዘንድ የላቀ ዕውቅናን ያላቸው እንዲሆኑ ማስቻልን እንደ ግብ ማስቀመጡ ተመላክቷል። ለዚህም ስኬት የፈረንሳይ መንግስት አስፈላጊውን የቴክኒክና የማቴሪያል ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን፣በተለይም ሰላም አስከባሪዎች በጦር ሜዳ የሚያጋጥሟቸውን የፈንጂ አደጋዎች የመከላከል አቅማቸውን ማሳደግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል። ይህ ስምምነት በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ወታደራዊ ዲፕሎማሲ መሠረት ያደረገ ነው። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ያላት ቀዳሚ ተሳትፎና አሁንም በሰላም አስከባሪ ብዛት ከዓለም ቀዳሚዎቹ ተርታ መሰለፏ ለትብብሩ መጠናከር በምክንያትነት ተጠቅሷል። ስምምነቱ ኢትዮጵያ ለዓለም ሰላምና ደህንነት የምታበረክተውን አስተዋፅኦ ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርገው ተገልጿል። በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ዘላቂ ወዳጅነት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው መገለጹን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ማካሄድ ጀመረ
Mar 27, 2026 266
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀው የክርክር መድረክ መጪው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበልጥ አካታችና አሳታፊ እንዲሆን ለማድረግ ያለመ የመጀመሪያውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክር ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቦርዱ ባለፉት ጥቂት ወራት የክርክር መድረኩን ለማዘጋጀት ሲሰራ የቆየ ሲሆን፤ ይህም በኢትዮጵያ የምርጫ ሂደት ውስጥ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ብለዋል። ይህ ተነሳሽነት የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን አማራጭ የፖሊሲ ሃሳቦች ለሕዝብ የሚያቀርቡበት ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረው፤ ፓርቲዎቹ አቋማቸውን ለማሳወቅ እንደሚረዳና መራጩ ሕዝብ ያደገ ግንዛቤ እንዲኖረው አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል። እንደ ሰብሳቢዋ ገለጻ፤ ቦርዱ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ለመደገፍ የተለያዩ ስልጠናዎችን ጨምሮ ፓርቲዎች የሙከራ ክርክሮችን እንዲያካሄዱ የሚያስችል ዕድልንም ፈጥሯል። መድረኩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችን እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን በማገናኘት ለዲሞክራሲያዊ ምህዳር መስፋት አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም አብራርተዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደገለጹት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበልጥ አካታች እና አሳታፊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ እያደረገ ያለው ጥረት አካል ነው። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ምርጫ
የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ካርድ በማውጣት የሚበጃቸውን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገለጹ
Mar 27, 2026 156
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ በማውጣት ለሴቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚሠራ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ተናገሩ። እጸገነት ሙሉጌታ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሀገርንና የትውልድን ተስፋ ብሩኅ ለማድረግ ሴቶች በምርጫ ወቅት የሚያደርጉት ንቁ ተሳትፎ የጎላ ሚና አለው። ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ምዝገባ ማከናወናቸውንም ተናግረዋል። ማኅሌት ጥላሁን በበኩላቸው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብቶችን መጠቀም የሚያስችሉ ዕድሎችን ያሰፋና የሕዝቦችንም ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በር የከፈተ ነው ብለዋል። ይበጀኛል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸው፤ ዜጎች በምርጫ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ይመክራሉ። ሴቶች ለተሻለ ነገ በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይገባናል ያሉት ደግሞ ዝናሽ ቦጋለ ናቸው። ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን የምናረጋግጥበት መንገድ በመሆኑ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል ያሉት ደግሞ ሰናይት ቀበታ ናቸው።
የጥፋት ኃይሎችን በመታገል የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት መረባረብ ይገባል
Mar 27, 2026 194
ወልዲያ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- ለግጭት የሚጥሩ የጥፋት ኃይሎችን በመታገል የዘላቂ ሰላምና ልማት ዕቅዶቻችንን ለማሳካት መትጋት አለብን ሲሉ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ። ምክትል ርዕሰ መሥተዳድሩ በሰሜን ወሎ ዞን ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት በመሆኑ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ እየተሠራበት ነው ብለዋል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አብዱ (ዶ/ር)። ለሰላምና የልማት ሥራዎች የጸጥታ አካላት ብርቱ ጥረት እንዳለ ሆኖ፤ የሕብረተሰቡ ትብብርና ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና እንዳለም አስገንዝበዋል። በመሆኑም ለግጭትና ጦርነት የሚጥሩ የጥፋት ኃይሎችን በመታገል የዘላቂ ሰላምና ልማት ዕቅዶቻችንን ለማሳካት በጋራ መትጋት አለብን ብለዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አራጌ ይመር፤ የዞኑ ሕዝብ የሰላም ጥረትና ለልማት ያለው ትጋት የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የጥፋት ዓላማ ይዘው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች መንግሥት ባቀረበላቸው የሰላም ጥሪ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ መመለሳቸውን ገልጸው፤ በዚህ ጥረት ውስጥ የሕዝቡ እገዛ የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቀጣይም በየአካባቢው የሀገርን ጥቅም አሳልፈው ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ባንዳዎችን በጋራ መታገል እንደሚገባ አመላክተዋል።
የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 27, 2026 255
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ) ፦ የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል የሚከናወነውን የምክክር ሂደት አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመግለጫቸው፤ ኮሚሽኑ እስካሁን ሂደቱን አሳታፊ እና አካታች ለማድረግ ሲያከናውናቸው የቆዩ ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን ገልጸዋል። ስራዎቹም ከወረዳ ጀምሮ ህዝብን ባሳተፈ መልኩ ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል። በትግራይ ክልል የሚገኙ ዜጎች በምክክር ሂደቱ የመሳተፍ ሙሉ መብት እንዳላቸውና ለሂደቱ ውጤታማነትም በጎ አበርክቶ እንዳላቸው ገልጸዋል። ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ለመጀመርና ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ዋና ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው አስታውሰዋል። በዚህም ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀሌ እና በአዲስ አበባ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ጥረቶች ውስጥ በክልሉ ውስጥ ሂደቱን ለማካሄድ የሚያስችሉ አስቻይ ሁኔታዎች ባለመፈጠራቸው፤ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች ምርጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ እንዲከናወን መወሰኑን አስረድተዋል። በዚህም በክልሉ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። ሁሉም በየደረጃው የሚገኙ የባለድርሻ አካላት ከመጋቢት 23 ጀምሮ በሚከናወነው በዚህ ሂደት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ምክክር
ፖለቲካ
የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የአባል ሃገራቱን ጥቅም ለማስከበር መትጋት ይጠበቅበታል
Mar 27, 2026 297
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የተቋቋመለትን አላማ እንዲያሳካ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ነጻነቱን ጠብቆ መጓዝ እንደሚገባው በቤልጂየም፣ ኔዘርላንድስ እና ሉክስምበርግ (ቤኔሉክስ) አገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢትዮጵያ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ገለጹ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት (ኦ ኤስ ፒ ኤስ ) የመሪዎች ጉባኤ ነገ ይጀምራል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴን ጨምሮ በርካታ የሀገራት መሪዎች በጉባኤው ላይ ይሳተፋሉ። የድርጅቱ የመሪዎች ጉባኤ ቅድመ ስብስባ ዛሬ ተካሄዷል። በስብሰባው ላይ በቤልጂየም፣ ኔዘርላንድስ እና ሉክስምበርግ (ቤኔሉክስ) አገራት እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢትዮጵያ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ተገኝተዋል። አምባሳደር እሸቴ በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት ለአባል ሀገራቱም ሆነ ለመላው ዓለም ወሳኝ አስተዋጾኦ ማድረግ እንዲችል ራሱን በገንዘብ እና በመዋቅር ማጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል። አስቸጋሪ በሆነው የዓለም ተቀያያሪ የኢኮኖሚና ፖለቲካ ሁኔታ ውስጥ ድርጅቱ የአባል ሀገራቱ ጥቅም እንዲከበር በትጋት መስራት እንዳለበት አመልክተዋል። አምባሳደር እሸቴ በተለይ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ድርጅቱ እ.አ.አ በ1975 ከቅኝ ግዛት በኋላ የተመሰረተ እና በቅኝ ግዛት ሲጎዱ ለነበሩ የአፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት አለኝታ እንዲሆን ታስቦ የተመሰረተ መሆኑን አስታውሰው ኢትዮጵያ ለዚህ ድርጅት መጠናከር ትኩረት ሰጥታ እንደምትንቀሳቀስ አስረድተዋል። ባለፉት ጊዜያት የድርጅቱ በጀት በአውሮፓ ህብረት ድጋፍ ይሸፈን እንደነበረ ገልጸው ድርጅቱ የተቋቋመለትን አላማ እንዲያሳካ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ነጻነቱን ጠብቆ መጓዝ እንዳለበት አስገንዝበዋል። ለዚህ ደግሞ አባል ሀገራቱ የሚጠበቅባቸውን የገንዘብ መዋጮ መክፍል እንደሚገባቸው ነው ያሳሰቡት። በቅድመ ጉባኤ ስብሰባው የበርካታ ሀገራት ተወካዮች ድርጅቱ እያበረከተ ያለውን የማይተካ አስተዋጾኦ በማድነቅ የተሻለ ጠንካራ ሆኖ በሚወጣበት ጉዳይ ላይም ሀሳባቸውን ሰጥተዋል። በአባል ሀገሪቱ ያለውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ማሳደግ፣ የወጣቶችን አቅም በሚገባ መጠቀም ከዳያስፖራው ማህበረሰብ ጋር ያለን ትስስር በማሳደግ ለሁለንተናዊ እድገት መጠቀም የሚሉት በስፋት የተንሸራሸሩ ሀሳቦች ናቸው። በአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ያለውን ድህነት በማጥፋት ኢኮኖሚያዊ እድገትን ማፋጠንን አላማ በማድረግ የተመሰረተው ድርጅቱ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት አይነተኛ የትብብር ማዕከል ሆኖ እያገለገለ ነው። ከአውሮፓ ሀገራት ጋር ያለው የንግድ፣ ልማት፣ ዴሞክራሲ፣ አስተዳደር እና ሰብዓዊ ጉዳዮች ትብብር ደግሞ የደቡብ- ሰሜን ትስስርን በማጠናከር ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀው የክርክር መድረክ መራጩ ህዝብ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ድምፅ እንዲሰጥ ምቹ መደላድል ይፈጥራል
Mar 27, 2026 260
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀው ወጥ የሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ መራጩ ህዝብ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ድምፅ እንዲሰጥ ምቹ መደላድል እንደሚፈጥር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባዘጋጀው የመጀመሪያው የክርክር መድረክ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት(ሰላም)፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) ፓርቲ፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት እና ብልፅግና ፓርቲ ተሳትፈዋል። የክርክር መድረኩን አምስቱ የቦርዱ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በይፋ አስጀምረውታል። በዚሁ ወቅት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ የክርክር መድረኩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጭና ፕሮግራሞቻቸውን ነጻ፣ ገለልተኛና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለህዝብ የሚያደርሱበት ነው ብለዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን ለህዝብ የሚያደርሱበትን ወጥ የሆነ የክርክር መድረክ ለማመቻችት በርካታ የሙከራ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቀዋል። የክርክር መድረኩ መራጩ ህዝብ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚፎካከሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አማራጭ ሃሳቦች በማጤን በዕውቀትና በመረጃ ላይ የተመሰረተ ድምፅ እንዲሰጥ ማድረግ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል። በምርጫ ክርክር የዝግጅት ምዕራፉ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጫቸውን ለህዝብ የሚያደርሱባቸው ርዕሰ ጉዳዮች በገለልተኛ ሙያተኞች ጥናት መካሄዱንም አስታውሰዋል። በተጨማሪም በክሩክሩ ወቅት የሚቀርቡ አሃዛዊ መረጃዎችና ሀሳቦች ትክክለኝነት የሚመዝኑና የሚያጣሩ ባለሙያዎች እንዲካተቱ መደረጉንም አንስተዋል። በክርክር መድረኩም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች እንዲገኙ በማድረግ ለዲሞክራሲ ምኅዳር መጎልበት ከፍተኛ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አካታችነተና አሳታፊነትን ለማረጋገጥ የሚደረጉ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጩ ህዝብ በቀረቡት የማኑዋልና ዲጂታል አማራጮች ድምፅ መስጠት የሚያስችለውን ካርድ በስፋት እየወሰደ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የክርክር መድረኩም መራጩ ህዝብ ድምፅ መስጫ ካርድ እንዲወስድ ከፍተኛ መነቃቃት እንደሚፈጥር ሰብሳቢዋ ጨምረው ገልጸዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ተዘጋጅተናል
Mar 27, 2026 244
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። በዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች አስፈላጊ የምርጫ ቅድመ ዝግጅቶችም እየተከናወኑ ይገኛሉ። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ወጣቶች እንደገለጹት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት በዝግጅት ላይ ናቸው። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወጣት መዲና መሀመድ ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎች ላይ በመሳተፍ እንደ ዜጋ ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የሚጠበቅባትን ድርሻ መወጣቷን ገልጻለች። ዘንድሮ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ ማውጣቷን ገልጻ፤ የወጣቱን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለው ብላለች። ወጣት ኤርሚያስ ወንድሙ በበኩሉ፤ በምርጫው ወጣቱን ጨምሮ የዜጎችን ተጠቃሚነት ከፍ ወዳለ ደረጃ ለማሸጋገር ለሚሰራ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅቻለሁ ሲል ገልጿል። የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚችለውን ፓርቲ ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ ወስዶ በመጠባበቅ ላይ መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት ኢሳ ሰኢድ ነው፡፡ ሌላኛዋ ወጣት የተመኝ አስማማው በበኩሏ፤ ምርጫው የዲሞክራሲ መብት ተጠቃሚነትን የምናረጋግጥበት መንገድ በመሆኑ ያስተዳድረኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብላለች፡፡ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት በረከት ቢርቢርሳ፤ ማህበሩ ከዚህ ቀደም በነበሩ ምርጫዎች ላይ ወጣቶች የተሻለ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የማስተባበር ሚናውን ሲወጣ መቆየቱን አንስቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ለወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ በመስራት በምርጫው አስተዋጿቸውን እንዲያበረክቱ እየሰራ መሆኑን ተናግሯል፡፡
ኢትዮጵያና ፈረንሳይ በሰላም ማስከበር ዘርፍ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት የሚያጠናክር ስምምነት ተፈራረሙ
Mar 27, 2026 301
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ በሰላም ማስከበር ዘርፍ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስልታዊ አጋርነት ማሳደግ ያለመ የሁለትዮሽ ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ (ኢ/ር) እና በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ላሜክ ፈርመዋል፡፡ ስምምነቱ በዋናነት በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ የሚሰማሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላትን ኦፕሬሽናል ዝግጁነት ለማሳደግና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ብቃት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው። በስምምነቱ መሰረት፣ የዓለም አቀፍ የሰላም ድጋፍ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት (IPSTI) እና የኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት (CTS) የሚሰጡ የሥልጠና ሰርተፊኬቶች ዓለም አቀፍ ዕውቅና እና የምርምር ተግባራት ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ይደረጋል። በተጨማሪም ስምምነቱ የኢትዮጵያ የሰላም ማስከበር ማዕከል የሚሰጡ የስልጠና ሰርተፊኬቶች በተባበሩት መንግሥታትና በአፍሪካ ሕብረት ዘንድ የላቀ ዕውቅናን ያላቸው እንዲሆኑ ማስቻልን እንደ ግብ ማስቀመጡ ተመላክቷል። ለዚህም ስኬት የፈረንሳይ መንግስት አስፈላጊውን የቴክኒክና የማቴሪያል ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን፣በተለይም ሰላም አስከባሪዎች በጦር ሜዳ የሚያጋጥሟቸውን የፈንጂ አደጋዎች የመከላከል አቅማቸውን ማሳደግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል። ይህ ስምምነት በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ወታደራዊ ዲፕሎማሲ መሠረት ያደረገ ነው። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ያላት ቀዳሚ ተሳትፎና አሁንም በሰላም አስከባሪ ብዛት ከዓለም ቀዳሚዎቹ ተርታ መሰለፏ ለትብብሩ መጠናከር በምክንያትነት ተጠቅሷል። ስምምነቱ ኢትዮጵያ ለዓለም ሰላምና ደህንነት የምታበረክተውን አስተዋፅኦ ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርገው ተገልጿል። በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ዘላቂ ወዳጅነት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው መገለጹን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ማካሄድ ጀመረ
Mar 27, 2026 266
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀው የክርክር መድረክ መጪው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበልጥ አካታችና አሳታፊ እንዲሆን ለማድረግ ያለመ የመጀመሪያውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክር ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቦርዱ ባለፉት ጥቂት ወራት የክርክር መድረኩን ለማዘጋጀት ሲሰራ የቆየ ሲሆን፤ ይህም በኢትዮጵያ የምርጫ ሂደት ውስጥ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ብለዋል። ይህ ተነሳሽነት የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን አማራጭ የፖሊሲ ሃሳቦች ለሕዝብ የሚያቀርቡበት ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረው፤ ፓርቲዎቹ አቋማቸውን ለማሳወቅ እንደሚረዳና መራጩ ሕዝብ ያደገ ግንዛቤ እንዲኖረው አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል። እንደ ሰብሳቢዋ ገለጻ፤ ቦርዱ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ለመደገፍ የተለያዩ ስልጠናዎችን ጨምሮ ፓርቲዎች የሙከራ ክርክሮችን እንዲያካሄዱ የሚያስችል ዕድልንም ፈጥሯል። መድረኩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችን እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን በማገናኘት ለዲሞክራሲያዊ ምህዳር መስፋት አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም አብራርተዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደገለጹት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበልጥ አካታች እና አሳታፊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ እያደረገ ያለው ጥረት አካል ነው። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ምርጫ
የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ካርድ በማውጣት የሚበጃቸውን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገለጹ
Mar 27, 2026 156
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ በማውጣት ለሴቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚሠራ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ተናገሩ። እጸገነት ሙሉጌታ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሀገርንና የትውልድን ተስፋ ብሩኅ ለማድረግ ሴቶች በምርጫ ወቅት የሚያደርጉት ንቁ ተሳትፎ የጎላ ሚና አለው። ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ምዝገባ ማከናወናቸውንም ተናግረዋል። ማኅሌት ጥላሁን በበኩላቸው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብቶችን መጠቀም የሚያስችሉ ዕድሎችን ያሰፋና የሕዝቦችንም ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በር የከፈተ ነው ብለዋል። ይበጀኛል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸው፤ ዜጎች በምርጫ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ይመክራሉ። ሴቶች ለተሻለ ነገ በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይገባናል ያሉት ደግሞ ዝናሽ ቦጋለ ናቸው። ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን የምናረጋግጥበት መንገድ በመሆኑ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል ያሉት ደግሞ ሰናይት ቀበታ ናቸው።
የጥፋት ኃይሎችን በመታገል የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት መረባረብ ይገባል
Mar 27, 2026 194
ወልዲያ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- ለግጭት የሚጥሩ የጥፋት ኃይሎችን በመታገል የዘላቂ ሰላምና ልማት ዕቅዶቻችንን ለማሳካት መትጋት አለብን ሲሉ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ። ምክትል ርዕሰ መሥተዳድሩ በሰሜን ወሎ ዞን ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት በመሆኑ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ እየተሠራበት ነው ብለዋል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አብዱ (ዶ/ር)። ለሰላምና የልማት ሥራዎች የጸጥታ አካላት ብርቱ ጥረት እንዳለ ሆኖ፤ የሕብረተሰቡ ትብብርና ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና እንዳለም አስገንዝበዋል። በመሆኑም ለግጭትና ጦርነት የሚጥሩ የጥፋት ኃይሎችን በመታገል የዘላቂ ሰላምና ልማት ዕቅዶቻችንን ለማሳካት በጋራ መትጋት አለብን ብለዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አራጌ ይመር፤ የዞኑ ሕዝብ የሰላም ጥረትና ለልማት ያለው ትጋት የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የጥፋት ዓላማ ይዘው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች መንግሥት ባቀረበላቸው የሰላም ጥሪ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ መመለሳቸውን ገልጸው፤ በዚህ ጥረት ውስጥ የሕዝቡ እገዛ የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቀጣይም በየአካባቢው የሀገርን ጥቅም አሳልፈው ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ባንዳዎችን በጋራ መታገል እንደሚገባ አመላክተዋል።
የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 27, 2026 255
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ) ፦ የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል የሚከናወነውን የምክክር ሂደት አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመግለጫቸው፤ ኮሚሽኑ እስካሁን ሂደቱን አሳታፊ እና አካታች ለማድረግ ሲያከናውናቸው የቆዩ ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን ገልጸዋል። ስራዎቹም ከወረዳ ጀምሮ ህዝብን ባሳተፈ መልኩ ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል። በትግራይ ክልል የሚገኙ ዜጎች በምክክር ሂደቱ የመሳተፍ ሙሉ መብት እንዳላቸውና ለሂደቱ ውጤታማነትም በጎ አበርክቶ እንዳላቸው ገልጸዋል። ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ለመጀመርና ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ዋና ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው አስታውሰዋል። በዚህም ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀሌ እና በአዲስ አበባ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ጥረቶች ውስጥ በክልሉ ውስጥ ሂደቱን ለማካሄድ የሚያስችሉ አስቻይ ሁኔታዎች ባለመፈጠራቸው፤ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች ምርጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ እንዲከናወን መወሰኑን አስረድተዋል። በዚህም በክልሉ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። ሁሉም በየደረጃው የሚገኙ የባለድርሻ አካላት ከመጋቢት 23 ጀምሮ በሚከናወነው በዚህ ሂደት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ምክክር
ማህበራዊ
ለየጤና ነገር …
Mar 27, 2026 101
ስለ ሄርኒያ (ቡዓ) ምን ያህል ግንዛቤ አለዎት? ሄርኒያ ምንድን ነው? መንስዔውስ? በዚህ ጉዳይ ላይ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የሕጻናት ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ካሳሁን ግርማ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ሙያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። • ምንነት እንደ ዶክተር ካሳሁን ገለጻ፤ ሄርኒያ (ቡዓ) ማለት በሆድ ግድግዳ ላይ ባለ ክፍተት ወይም በሆድ ግድግዳ መሳሳት ምክንያት ሆድ ውስጥ ያሉ የሰውነት ክፍሎች በዋናነት አንጀት ከተፈጥሯዊ ቦታው ሲወጣ ማለት ነው። በአብዛኛው አዲስ የተወለዱ ሕጻናትን ይይዛል፤ አንዳንድ ጊዜም ቆይቶ ሊከሰት ይችላል የሚሉት ባለሙያው፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘም እስከ 6 በመቶ የሚወለዱ ወንድ ሕጻናት የሄርኒያ ሰርጀሪ እንደሚያስፈልጋቸው ጥናቶች ያመላክታሉ ብለዋል። • መንስዔ መንስዔው እንደታካሚው ዕድሜ ይወሰናል ያሉት ዶክተር ካሳሁን፤ በአጠቃላይ መንስዔዎቹ የሆድ ግድግዳ ክፍተት እና የሆድ ግድግዳ መሳሳት መሆናቸውን ያስረዳሉ። በዚህም መሠረት በአብዛኛው ሕጻናት ላይ በዋናነት በተፈጥሮ ያለውን የሆድ ግድግዳ ክፍተት በመጠቀም ዐዋቂዎች ላይ ደግሞ የሆድ ግድግዳ በሚሳሳበት ጊዜ አንጀት አፈትልኮ ከተፈጥሯዊ ቦታ ይወጣል ይላሉ። • ምልክቶች ሕጻናት እንደተወለዱ በደንብ በሕክምና ባለሙያ ሊታዩ እንደሚገባ የሚመክሩት ዶክተር ካሳሁን ከሄርኒያ ምልክቶች መካከል፤ በታችኛው የሆድ ክፍል አካባቢ ወይም የዘር ፍሬ ከረጢት የተለየ ዕብጠት መታየት፣ ዕብጠቱ አንዳንድ ጊዜ በራሱ የሚጠፋ ወይም ደግሞ በዕጅ በሚነካበት ጊዜ ወደ ውስጥ የሚገባ ሊሆን ይችላል፣ አንዳንድ ጊዜ ወጥቶ የማይመለስ (ወደ ውስጥ የማይገባ) ዓይነት ዕብጠት ሆኖ የሆድ መነፋት መከሰት እንዲሁም ሀሞት የቀላቀለ ማስመለስ የሚሉት እንደሚገኙበት አብራርተዋል። • ሕክምና ሕክምናው በዋናነት መንስዔውን ማከም መሆኑን አስገንዝበው፤ በዚህም መሠረት መንስዔው የሆድ ግድግዳ ላይ ያለ ክፍተት ወይስ የሆድ ግድግዳ መሳሳት የሚለውን መለየት የሕክምናው አካል መሆኑን አስረድተዋል። ከዚያም አንጀት እንዳይወጣ የሆድ ግድግዳ ላይ ያለውን ክፍተት ወይም የሆድ ግድግዳ መሳሳት በቀዶ ሕክምና ማካም እንደሚቻል አረጋግጠዋል። በተፈጠረው ክፍተት አንጀት የሚወጣ እና በራሱ የማይመለስ ከሆነ በተለይም በዕጅ በሚነካበት ሠዓት ወደ ሆድ ዕቃ ውስጥ (ወደ ተፈጥሯዊ ቦታው) ካልተመለሰ የአንጀት ደም ዝውውር ስለሚስተጓጎል ጋንግሪን የመሥራት፣ የተሠራጨ ኢንፌክሽን መኖር እንዲሁም እስከ ሞት ሊያደርስ ስለሚችል ለሕክምና ቅድሚያ መስጠትን መክረዋል ባለሙያው።
በውጭ ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ቅርሶችን የማስመለሱ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Mar 27, 2026 96
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦በውጭ ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ቅርሶችን የማስመለሱ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ገለጸ። ባለስልጣኑ በመቅደላ ጦርነት ጊዜ ከመቅደላ ተዘርፎ ከ150 አመታት በላይ ያስቆጠረውን ከወርቅ የተሰራ የአፄ ቴዎድሮስ ባለቤት የእቴጌ ጥሩወርቅ ውቤ የፀጉር ጌጥ ( ወለባ) የኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር አባላት፣ እና ሌሎች አካላት በተገኙበት የርክክብ መርሃ ግብር አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው እንደተናገሩት፤ ባለፉት ዓመታት በውጭ ሀገራት የሚገኙ ቅርሶችን የማስመለስ ስራዎች በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። ከ72 በላይ ቅርሶችን በበጎ ፍቃደኝነት፣ በትብብርና በድርድር ማስመለስ መቻሉን ገልጸው፤ ለሀገር ውስጥና ውጭ ጉብኚዎች እንዲበቁም ተደርጓል ብለዋል። ከውጭ ሀገራት የተመለሱ ቅርሶችን የሚታዩበት ክፍል የማዘጋጀት ስራዎችን እስከ ሰኔ 2018 ዓም ድረስ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት በርካታ ቅርሶች የሚገኙ በመሆኑ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የሚሰሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። በውጭ ሀገራት የሚገኙ የሚታወቁ ቅርሶችን ቆጠራ ማድረግ፣ መመዝገብና ዲጂታላይዝ በማድረግ የማስመለስ ጥረቱን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ኮሚቴ የቦርድ አባል አሉላ ፓንክረስት (ዶ/ር) የእቴጌ ጥሩወርቅ ውቤ የፀጉር ጌጥ ላይ ቅርሱ እ.ኤ.አ 1868 ከመቅደላ እንደተወሰደ በጽሁፍ መስፈሩን ይናገራሉ። ይህም ቅርስ ጣሊያን ሮም ላይ ለጨረታ ቀርቦ ጨረታውን በአጭር ጊዜ ማስቆም መቻሉን ነው የገለጹት። ቅርሱ ትልቅ ታሪክ ያለው መሆኑን ገልጸው፤ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመስራት ለማስመለስ መቻሉን አብራርተዋል። የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያን ቅርሶች ለማስመለስ መተባበርና የበለጠ በጋራ በመሰራት ያስፈልጋል ብለዋል። ለትውልዱ የሀገሪቱን ትልቅነት ታሪክ ለማስተማር ቅርሶች ጉልህ አሰተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል።
ጥራቱ የተረጋገጠ መድኃኒት ለማኅበረሰቡ የማቅረብ ሥራ እየተከናወነ ነው
Mar 27, 2026 99
አርባምንጭ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- ጥራትና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ መድኃኒቶችን ለማኅበረሰቡ የማቅረብ ሥራ በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። 8ኛው የጤና ዘርፍ የባለድርሻ አካላት ምክክር መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው። የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ፍሬሕይወት አበበ በዚሁ ወቅት፤ የአሠራርና የአደረጃጀት ሥራዎችን በማሻሻል የመድኃኒት አቅርቦት ጥራትና ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተሠራ ነው ብለዋል። መድኃኒቶችን በተገቢው መንገድ መጠቀም በተለይ መድኃኒት የተላመዱ በሽታዎች የሚያደርሱትን ጫና ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል። ከ53 ሺህ በሚልቁ የጤና ተቋማት ፈዋሽነቱ የተረጋገጠ የመድኃኒት አቅርቦት ሥርዓት እንዲኖር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አብዱልቃድር ጋልጋሎ (ዶ/ር) ፈዋሽነቱና ደኅንነቱ የተረጋገጠ መድኃኒት ለማኅበረሰቡ እንዲዳረስ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲሠራ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በዲጂታል ሥርዓት በመታገዝ አቅርቦቱን ይበልጥ ለማሳለጥ እንደሚሠራ አመላክተዋል። በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት 64 ቢሊየን ብር የሚገመቱ መድኃኒቶችና የሕክምና መገልገያዎች ለጤና ተቋማት መሰራጨታቸውንም አረጋግጠዋል።
ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናት የልጅነት ልምሻ ክትባት እየተሰጠ ነው
Mar 27, 2026 83
ቦንጋ፣ ደብረ ብርሃን፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ 5ኛው ዙር የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) ክትባት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ዛሬ መሰጠት ጀምሯል። በዚህም መሠረት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ኢብራሂም ተማም በቦንጋ ከተማ ሸታ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው የክትባት ዘመቻውን አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም መንግሥት የበለጸገና ጤናማ ዜጋን ለመፍጠር ከሚሠራቸው ሥራዎች መካከል አንዱ የክትባት አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ ነው ብለዋል። ክትባት ሕጻናት በአዕምሮና በአካል ጤናማ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እንዳለው ገልጸው፤ ይህም በመደበኛና በዘመቻ መልክ እየተካሄደ መሆኑን አረጋግጠዋል። ከፖሊዮ ክትባት በተጨማሪ የአፈጣጠር ችግር ያለባቸውን ሕጻናት፣ ከወሊድ ጋር የተያያዘና ፌስቱላን የመሳሰሉ ችግሮች ያሉባቸው እናቶች ልየታና ወደ ሕክምና የመላክ ሥራ እንደሚሠራ ተናግረዋል። የአማራ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ስሜነህ አያሌው ደግሞ በደብረ ብርሃን ከተማ የፖሊዮ ክትባትን አስጀምረዋል። የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻውን ለመስጠት 12 ሺህ 501 ባለሙያዎችን በማሳተፍ በትምህርት ቤቶች፣ በቤት ለቤትና በጤና ተቋማት መሰጠት መጀመሩን አስታውቀዋል። ማኅበረሰቡም በአካባቢው የሚገኙ ሕጻናትን በማስከተብ ከበሽታው ለመጠበቅ የሚደረገውን ጥረት እንዲያግዝ ጠይቀዋል።
ኢኮኖሚ
“ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2026” ፎረም በ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ውሎች ፊርማ ተጠናቀቀ
Mar 27, 2026 193
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አራተኛው “ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2026” ፎረም ዛሬ ተጠናቋል። በፎረሙ ላይ የተለያዩ ዋና ዋና ዘርፎችን ያካተቱና በአጠቃላይ 13 ነጥብ 1 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚገመቱ የኢንቨስትመንት ውሎች ተፈርመዋል። በፎረሙ መጨረሻ የተከናወነው የፊርማ መርሃግብር በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና እና አግሮ-ፕሮሰሲንግ፣ በኃይል፣ በማዕድንና በሌሎች ዘርፎች ትልልቅ የኢንቨስትመንት ስምምነቶችን ያካተተ ነው። የተፈረሙት ውሎች በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ያለውን የኢንቨስተሮች እምነት እንደሚያሳይ ተገልጿል። በተጨማሪም ለስራ ፈጠራ፣ ለውጭ ምንዛሬ ግኝትና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ተጠቅሷል። በተመሳሳይ በ“ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2025” ፎረም በአጠቃላይ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር የሚገመቱ የኢንቨስትመንት ውሎች መፈረማቸው የሚታወስ ሲሆን እነዚህም ፕሮጀክቶች አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ መግባታቸው ይታወቃል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ እንደ ግንባር ቀደም የኢንቨስትመንት መዳረሻ እየታየች መሆኗን ያመላክታል። ፎረሙ አዳዲስ አጋርነቶችን ለመፍጠርና ቀጣይ የኢንቨስትመንት ግንኙነቶችን ለማጎልበት ጠንካራ መድረክ መሆኑን መረጋገጡን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
መንግሥት ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም አሳድጓል
Mar 27, 2026 92
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሰጠው ከፍተኛ ትኩረትና እያደረገ ያለው ድጋፍ የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ማሳደጉን የተለያዩ አምራቾች ገለጹ። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተማ የሚገኙ የጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ የቆዳ፣ የምግብና በኤሌክትሮኒክስ ግብዓቶች አምራች ኢንዱስትሪዎችን የመስክ ምልከታ አድርገዋል። በመስክ ምልክታው መንግስት ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤቶችን የተመዘገቡ ሲሆን ዘርፉ ለውጭ ምንዛሬ ግኝት፣ ለተኪ ምርትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ወሳኝ ድርሻ ያለው መሆኑ በዚሁ ወቅት ተጠቁሟል፡፡ የኒው ዊንግ አዲስ ጫማና ቆዳ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ ኢቫኖ መስፍን በዚሁ ወቅት፤ ኒው ዊንግ አዲስ ለ16 ዓመታት በቆዳና ጫማ ምርት ዘርፍ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ በቆይታው ያካበተውን ልምድ ተጠቅሞ ያመረታቸውን ምርቶች ለሰሜን አሜሪካ ገበያ በስፋት እያቀረበ እንደሚገኝ አመላክተዋል። በዘርፉ በዓለም ላይ ካሉ ግዙፍ ኩባንያዎች ጋር ተወዳዳሪ መሆን የቻልነው በመንግስት በኩል ለላኪዎች የሚደረገው የፋይናንስና የሎጂስቲክስ ድጋፍ በመኖሩ ነው ብለዋል። ቡም ማኑፋክቸሪንግ የተባለ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ፀጋ ደበበ በበኩላቸው፤ ድርጅታቸው የተለያዩ ማቀዝቀዣዎችን በማምረት በኩል ትልቅ እመርታ ማሳየቱን ተናግረዋል። በተለይም ከውጭ የሚመጡ ቴክኖሎጂዎችንና ዕውቀቶችን በሀገር ውስጥ በማስረጽ ውጤታማ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። እስካሁን ለ400 ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ተናግረው፤ መንግስት እያደረገ ያለው ድጋፍ በተኪ ምርት ላይ ተጨባጭ ውጤት እንዲያመጡ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ የቦኤዝ የምግብ ኮምፕሌክስ ባለቤት ዮሴፍ ታደሰ በበኩላቸው መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ከፍተኛ ትኩረት ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡ በተለይም በግብርናው ዘርፍ በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገው ጥረት ለፋብሪካቸው ግብዓት በማቅረብ በኩል ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግስት በኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትና ለማስፋፊያ የሚሆን መሬት ለማመቻቸት እያደረገ ያለው ድጋፍ የምርት አቅማቸውን ይበልጥ እያጠናከረ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
በመዲናዋ ተረጂነትን በመቅረፍ ዜጎች በሀገር ግንባታ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች ውጤቶች ተመዝግበዋል
Mar 27, 2026 96
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ ተረጂነትንና ጥገኝነትን በመቅረፍ ዜጎች በሀገር ግንባታ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች ውጤቶች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ በምግብ ዋስትና እና ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም በርካታ ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር ዛሬ መርቀዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፤ ባለፉት ጥቂት አመታት ከ695ሺህ በላይ ዝቅተኛ እና ምንም ገቢ ያልነበራቸው ዜጎችን በሴፍትኔት ፕሮግራም በማካተት ከተረጂነት ወደ አምራችነት ማሸጋገር ተችሏል ብለዋል፡፡ እነዚህ ወገኖች በአሁኑ ወቅት ከራሳቸው አልፈው ቤተሰቦቻቸውንና ሀገራቸውን መርዳት መጀመራቸውን ጠቁመው የዛሬ ተመራቂዎችም በየአካባቢያቸው ተለይተው በተለያዩ ድርጅቶች የስራ ላይ ልምምድ ሲያደርጉ የቆዩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ይህ ፕሮግራም ወጣቶችን ራሳቸውን በማስቻል የምግብ ዋስትናንና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ሀገራዊ ጥረት አካል መሆኑን ገልጸዋል። ወጣቶቹ በስልጠና ቆይታቸው የህይወት ክህሎትን ጨምሮ የተለያዩ የሙያ ስልጠናዎችን እንዳገኙ ገልጸው ከተረጅነት ወደ አምራችነት ለሚደረግው ሽግግር ትልቅ አቅም እንደሚሆኑም ጠቁመዋል። ተረጂነትንና ጥገኝነትን በማስቀረት ዜጎች በሀገር ግንባታ ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች ውጤቶች መመዝገባቸውን ከንቲባዋ ተናግረዋል፡፡ የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ወጣቶችን ከተረጂነት ስሜት አውጥቶ ወደ ምርታማነት እያሸጋገር እንደሚገኝና ወጣቶች ለመቀጠርም ሆነ በራሳቸው ስራ ፈጥረው ለመስራት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ገልጸዋል፡፡ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚደረገው ሽግግር ብልጽግናን ፈጥኖ እውን በማድረግ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አይነተኛ ሚና እንደሚጫዎትም አመላክተዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ፤ የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራሙ ወጣቶች ለሀገር ኩራት ወደሚሆኑበት ደረጃ አሸጋግሯቸዋል ብለዋል፡፡ ከሰልጣኞች መካከል ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት ፎዚያ አወል፣ ነጻነት እና አሸብር እንዳሻው፤ በመረጥነው የስራ ሙያ ሰልጥነን አሁን ላይ ከቤተሰብ ጥገኝነት ተላቀን የራሳችን ገቢ መፍጠር ችለናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ለ2018/19 ለበልግ እና መኸር እርሻ የሚውል የአፈር ማዳበሪያ እየተሠራጨ ነው
Mar 27, 2026 99
ጅማ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- ለ2018/19 ለበልግ እና ለመኸር እርሻ የሚውል 470 ሺህ ኩንታል የዳፕ እና ዩሪያ የአፈር ማዳበሪያ እየተሠራጨ መሆኑን የጅማ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ገለጹ። በበልግ እና በመኸር እርሻ 880 ሺህ ሔክታር መሬት በዘር ለመሸፈን የመሬት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፤ በዘር ከሚሸፈነውም ከ35 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን ጠቁመዋል። በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያ በኅብረት ሥራ ማኅበራት በኩል ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑንም ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በዚህም መሠረት ለ2018/19 ለበልግ እና ለመኸር እርሻ የሚውል 920 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ መታቀዱን ጠቅሰው፤ እስካሁን 470 ሺህ ኩንታል የዳፕ እና ዩሪያ ማዳበሪያ እየተሠራጨ መሆኑን ገልጸዋል። ቀሪውም በአጭር ጊዜ እንደሚቀርብ አመላክተዋል። በሌላ በኩል በ1 ሺህ 900 ሔክታር ላይ ምርጥ ዘር ተባዝቶ ለአርሶ አደሩ በጊዜ እንዲቀርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኢኮኖሚው ምሶሶ እንዲሆን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር አለባቸው
Mar 27, 2026 255
ሮቤ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ ሳይንስና ቴክኖሎጂ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ መሪ ሚና እንዲጫወት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ ፈጠራና ኢንተርፕረነርሺፕ ላይ አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችና ግኝቶች ላሏቸው ወጣቶች ሲሰጥ የቆየውን ተግባር ተኮር ሥልጠና በማጠናቀቅ የእውቅና መርሐ ግብር አካሄዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ሳይንስና ቴክኖሎጂ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ መሪ ሚና እንዲጫወት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምርምር የመደገፍ ተግባራቸውን ማጠናከር ይገባቸዋል። ሚኒስቴሩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የኢኮኖሚው ምሶሶ እንዲሆን በሀገር ደረጃ የተቀረጸውን ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አክለዋል። በተለይ ክህሎትና አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብና ግኝት ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር ፕሮጀክቶቻቸው በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጣ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽንና የፈጠራ ምህዳርን በማስፋትና በዘርፉ የዳበረ ማህበረሰብ በመፍጠር ረገድ በተከናወኑ ሥራዎች አበረታች ለውጦች መታየታቸውን አመልክተዋል። በተለይ ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያበረታታ "ስታርት አፕ አክት" የተሰኘ የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖረውና የፋይናንስ ድጋፍ በማግኘት ወደ ኢኮኖሚ እንዲቀየር እየተደረገ መሆኑን በማሳያነት አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም በሀገር አቀፍ ደረጃ ባለፉት ዓመታት በዘርፉ የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ በማጠናከር ከወቅቱ ዓለም ዓቀፋዊ ሁኔታ ጋር የተናበበና በዘርፉ እመርታዊ ለውጥ ለማምጣት ያለመ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ ከመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችና ግኝቶች ላሏቸው ወጣቶች ያዘጋጀው የእውቅና መድረክ የዚሁ ጥረት አካልና ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ዩኒቨርሲቲው በባሌ፣ በምስራቅ ባሌና በምዕራብ አርሲ ዞኖች በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቴክኖሎጂ ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች በመመልመል የክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም በዩኒቨርሲቲው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል ሥልጠና ያገኙ ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በ2017 ዓ.ም በተካሄደው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውድድር አንደኛ ደረጃን በመያዝ ሽልማትና እውቅና ማግኘታቸው የዘርፉ ትኩረት ውጤት መሆኑን ለአብነት አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብና ግኝት ያላቸው ግለሰቦች በሥራቸው ስኬታማ እንዲሆኑና ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ተግዳሮቶችን እንዲረዱ የተሰጠው የአቅም ግንባታ ሥልጠና የጥረቱ አካል መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አክለዋል። እውቅና ያገኙ የፈጠራ ባለቤት የሆኑ ወጣቶች በበኩላቸው ያገኙት ተጨማሪ ዕውቀትና እውቅና የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሳቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ወጣቶች የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ የኢትዮጵያን የወደፊት ዕጣ ፋንታ እንዲወስኑ በትምህርት ዝግጁ ማድረግ ያስፈልጋል
Mar 27, 2026 132
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ወጣቶች የዓለምን ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ነባራዊ ሁኔታ በመረዳት የሀገሪቷን የወደፊት ዕጣ ፋንታ እንዲወስኑ በትምህርት ዝግጁ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ፡፡ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቆይታ ዓለም አቀፍ ተቋማት የደረሰባቸውን አደጋ፣ የርዕዮተ ዓለምና የሀያላት አሰላለፍ ለውጥ፣ የቴክኖሎጂ ልህቀት በአፍሪካ ላይ የሚያመጣውን ተጽዕኖና ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ሚኒስትሩ በቆይታቸው የዓለም ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ነባራዊ ሁኔታ ለታዳጊ ሀገራት ፈታኝ መሆኑን በማንሳት፤ አስቸኳይና ወሳኝ ርምጃ ይፈልጋል ብለዋል፡፡ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካውያን የህልውና ጥያቄ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ችግሩን ለመቋቋም ስልታዊ እሳቤና ዝግጅት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡ ፈተናዎችን ተጋፍጦ ለድል የሚበቃ ትውልድ ለመፍጠር ለሁኔታዎች የማይበገር የትምህርት ስርዓት መገንባት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያውያን ብሎም አፍሪካውያን ማድረግ የምንችለው ትልቁ ነገር የቀጣዩን ትውልድ በትምህርት በሚገባ ማዘጋጀት ነው ብለዋል፡፡ አፍሪካ በትምህርት ራሷን ለማዘጋጀት የቀጣዩን 50 ዓመት ልትጠቀምበት ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ፤ በትምህርት ስርዓቱ ላይ መሰረታዊ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ የዓለምን ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ነባራዊ ሁኔታ ተቋቁሞ የኢትዮጵያን መፃኢ ዕድል ለመወሰን የተሟላ እውቀት፣ ብቁና ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን መላመድ የሚችል ትውልድ መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ ሪፎርም በማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን በማስፋፋት፣ የትምህርት መሰረተ ልማት በመገንባት፣ የሥርዓት ትምህርት ማሻሻያና ጥራት ማረጋገጫ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ይሄውም ቀጣዩን ትውልድ የማብቃት አካል መሆኑን ገልጸው፤ በራሱ የሚተማመን ሀገርን የሚጠብቅና አፍሪካ ወደፊት ሊደርስባት ከሚችል አደጋ የሚከላከል ዜጋ መፍጠር ያስችላል ብለዋል፡፡ ትምህርት የትውልድ የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት የሰጡት ሚኒስትሩ፤ ችግሩን ቀለል አድርጎ ማየት እንደማይገባ ገልጸዋል፡፡ ትምህርት ወጣቶች የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ አመዛዝነው እንዲረዱና የሌሎችን ከመኮረጅ ይልቅ በሀገር በቀል እሳቤ አዳዲስ ሀሳቦችን እንዲያመነጩ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል፡፡ ለዚህም በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ በፖለቲካ፣ በፍልስፍናና በሌሎችም ዘርፎች ዓለም የሚያደርሰውን አሉታዊ ተፅዕኖ ተቋቁመው ማሻገር የሚችሉ ብቃት ያላቸው አመራሮችን ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ትምህርት ከአካዳሚክ እውቀት ባለፈ እሴቶችንና ማህበራዊ ንቃተ ህሊናን ማካተት እንዳለበት ገልጸው፤ ትምህርት ቀጣዩን ትውልድ ለማዘጋጀትና ለማስተማር ትምህርት የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የፖሊሲ አውጭዎች በወጣቶች ትምህርት ላይ መሰማራት የማህበራዊ ግብ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ ስትራቴጂያዊ ጉዳይ መሆኑን መረዳት አለባቸው ብለዋል፡፡
የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን ለመግታት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ሥርዓት እየተዘረጋ ነው
Mar 27, 2026 102
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018(ኢዜአ)፦ የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን ለመግታት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥር ሥርዓት እየተዘረጋ መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን አስመልክቶ በወጣው ዓመታዊ ሪፖርት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ለውጡን ተከትሎ የሀሳብ ነፃነት፣ ብዝሃነትና አካታችነት ተፈጥሯል፡፡ ዜጎች በተለያዩ አማራጮች መረጃ የሚያገኙበትና ሀሳባቸውን በነጻነት የሚያንሸራሽሩበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይህንን መልካም ዕድል በአዋጅና በመመሪያ በመደገፍ ለዴሞክራሲና ለሀገር ግንባታ ለማዋል እየተሰራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። ባለስልጣኑ ከሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት ጋር በተያያዘ በተለያዩ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ጥናት ሲያደርግ ቆይቷል ነው ያሉት፡፡ የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ለብሔራዊ ደህንነትና ለሀገር ሰላም፤ ለብዝሀነትና እኩልነት እንዲሁም ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አደጋ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ባለፉት ዓመታት የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል ጥናት በማካሄድ የመፍትሄ እርምጃ ሲወሰድ ቆይቷል ብለዋል፡፡ ባለስልጣኑ በተሰጠው ሃላፊነት መሰረት ማህበራዊ ሚዲያዎች የጥላቻ ንግግር እና የሀሰት መረጃዎችን ሪፖርት በቀረበላቸው በ24 ሰዓት ውስጥ እንዲያነሱ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በዘንድሮ ዓመት ከጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ጋር በተያያዘ የማህበራዊ ሚዲያዎች ግዴታና ሃላፊነታቸውን የተወጡበትን መንገድ የሚያሳይ ሪፖርት መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡ ዓመታዊ ሪፖርቱ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተከታይ ባላቸውና ከፍተኛ ይዘት በሚሰራጭባቸው አምስት የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆች ትኩረት ማድረጉን ጠቅሰዋል። በአምስት ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች በቴክኖሎጂ በታገዘ የህዝብ አስተያየት መጠይቅ ተሰብስቦ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መተንተኑን ገልጸዋል፡፡ በተለይ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ታግዘው የሚሰራጩ የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ ይዘቶች ስጋት መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ ይዘቶች በሀገር ሰላምና ልማት፣ በዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ላይ ስጋት እንዳይፈጥሩ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩም አሳስበዋል፡፡
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የመንግስት አገልግሎቶችን ፈጣን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ ለማድረግ እያገዘ ነው
Mar 25, 2026 104
ባህር ዳር፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የመንግስት አገልግሎቶችን ፈጣን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለመስጠት እያስቻለ መሆኑን የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። ዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በብሔራዊ ደረጃ የሚያገኙበት ሕጋዊና መሠረታዊ የመታወቂያ ዓይነት መሆኑም ይታወቃል። የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ የቻለ ይግዛው ለኢዜአ እንዳሉት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች በየደረጃው ፈጣንና ፍትኃዊ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እያስቻለ ነው ። በተለይም መታወቂያውን ከባንክና ሌሎች አሰራሮች ጋር በማስተሳሰር ወጥ የሆኑ አገልግሎቶችን በፍጥነትና በፍትሃዊነት ለማቅረብ እያገዘ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በክልሉ ቀልጣፋ አገልግሎቶችን ለመስጠት ከማስቻሉ ባሻገር ህገ- ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የራሱ ድርሻ እንዳለውም ጠቅሰዋል። በተያዘው ዓመትም ከ4 ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ መቻሉንም ነው ያመለከቱት። ፋይዳ የዜጎች ትክክለኛ ማንነት የሚገልፅ መሆኑን አመልክተው ደሕንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ ወሳኝ ድል ተቀዳጀች
Mar 27, 2026 126
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፦ በ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ያለው ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ከነዓን ማርክነህ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ዋልያዎቹ ብልጫ ወስደው ተጫውተዋል። የማጥቃት እንቅስቃሴያቸው ጥሩ የሚባል ነበር። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ድልድል የመግባት እድሏን አስፍታለች። የሁለቱ ሀገራት የመልስ ጨዋታ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ ስታዲየም ይካሄዳል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈ ወደ ምድብ ድልድል ማለፉን ያረጋግጣል። የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ በመጀመሪያ ጨዋታቸው ድል ቀንቷቸዋል። 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ጁን 2027 በታንዛንያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ ጣምራ አዘጋጅነት ይካሄዳል።
ጣልያን ዴንማርክ እና ስዊድን ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የጥሎ ማለፍ ፍጻሜ አለፉ
Mar 27, 2026 76
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የአውሮፓ ዞን የመጀመሪያ ዙር የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ማምሻውን ተደርገዋል። በቤርጋሞ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጣልያን ሰሜን አየርላንድን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ሳንድሮ ቶናሊ እና ሞይስ ኪን ጎሎቹን አስቆጥረዋል። በሌላኛው መርሐ ግብር ዴንማርክ ሰሜን ሜቄዶናያን 4 ለ 0 ረታለች። በፓርከን ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጉስታቭ ኢሳክሰን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ሚኬል ዳምስጋርድ እና ክርስቲያን ኖርጋርድ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ስዊድን ዩክሬንን 3 ለ 1 አሸንፋለች። በቫሌንሺያ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የአርሰናሉ አጥቂ ቪክቶር ዮኮሬሽ ሁለት ግቦችን በጨዋታ ቀሪውን ጎል በጨዋታ በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ማትቪይ ፖኖማሬንኮ ለዩክሬን ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ፖላንድ በሮበርት ሎዋንዶውስኪ እና ፒተር ዚሊኒሲኪ ጎሎች አልባኒያን 2 ለ 1 አሸንፋለች። አርበር ሆክስሃ ለአልባኒያ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በሌሎች ጨዋታዎች ኮሶቮ ስሎቫኪያን 4 ለ 3 ስትረታ ቼክ ሪፐብሊክ አየርላንድን፣ ቦሲኒያ እና ሄርዞጎቪና ዌልስን በተመሳሳይ በመለያ ምት አሸንፈዋል። ውጤቶቹን ተከትሎ ጣልያን፣ ዴንማርክ፣ ስዊድን፣ ፖላንድ ፣ ቼክ ሪፐብሊክ፣ ቦሲኒያ እና ሄርዞጎቪና እንዲሁም ኮሶቮ ለፍጻሜ ጨዋታ አልፈዋል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ቱርኪዬ ሮማንያን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ጣልያን ከቦሲኒያ እና ሄርዞጎቪና፣ ፖላንድ ከስዊድን፣ ቱርኪዬ ከኮሶቮ እና ዴንማርክ ከቼክ ሪፐብሊክ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ለዓለም ዋንጫው ለማለፍ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በጥሎ ማለፉ የሚያሸንፉ አራት ሀገራት አስቀድመው በቀጥታ ወደ ዓለም ዋንጫ ያለፉ 12 የአውሮፓ ሀገራትን ይቀላቀላሉ።
"ቪዚት ሐረር" የጎዳና ላይ የሩጫ ፌስቲቫል በሐረር ከተማ ተካሄደ
Mar 27, 2026 77
ሐረር፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- የሹዋሊድ በዓልን ምክንያት በማድረግ "ቪዚት ሐረር" የተሰኘ የጎዳና ላይ የሩጫ ፌስቲቫል በሐረር ከተማ ተካሂዷል። የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ፌስቲቫሉ፤ በርካታ የክልሉ ነዋሪዎች፣ አመራር አካላት፣ አትሌቶች፣ ታዳጊ ሕጻናት፣ ወጣቶችንና ሌሎችን አሳትፏል። የጎዳና ላይ የሩጫ ፌስቲቫሉን ያስጀመሩት የክልሉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ተውፊቅ መሀመድ እንዳሉት፤ የሩጫ ፌስቲቫሉ አብሮነትን የሚያጠናክር ነው። የሐረሪ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙራድ አብዲ በበኩላቸው፤ የሹዋሊድ በዓልን በማስመልከት የተዘጋጀው የሩጫ ፌስቲቫል በሐረር የሚገኙ የመስኅብ ስፍራዎችን ለማስተዋወቅና እንዲጎበኙ ለማድረግ ታስቦ መዘጋጀቱን አስረድተዋል። ይህም በክልሉ የሚገኙ ጥንታዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ የመስኅብ ስፍራዎችን ይበልጥ ለማስተዋወቅ ይረዳል ብለዋል። በፌስቲቫሉ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች የሜዳሊያና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቷል።
የስፖርት እንቅስቃሴ ባህልን የቀየሩት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች
Mar 27, 2026 77
በመዲናዋ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ስራዎች የከተማውን ገጽታ በመቀየር ውብ እንድትሆን እያደረጓት ይገኛሉ። በዚህም በርካታ መዝናኛ ስፍራዎችና ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ነው። እነዚህ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ቀንም ሆነ ማታ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሏቸው መሰረተ ልማቶች ተሟልተውላቸው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ያገኘናቸው ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ማዘውተሪያዎቹ በጀመሩት የምሽት አገልግሎት ከስራ መልስ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ጤናችን እንድንጠብቅ አስችሎናል። በከተማው የምሽት አገልግሎት መስጠት ከጀመሩት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መካከል በየካ ክፍለ ከተማ የሚገኝ 28 ሜዳ አንዱ ነው። በሜዳው ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ ወጣቶች መካከል ያሬድ ስጦታው ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ለበርካታ ዓመታት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት ሜዳ መሆኑን ገልጿል። ሜዳው ከዚህ ቀደም ጥራቱን ያልጠበቀና ምንም ዓይነት እድሳት ያልተደረገለት እንደነበርም ያስታውሳል። አሁን ግን ሜዳው ጥራቱን የጠበቀና ምሽትን ጨምሮ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሰረተ ልማት ተሟልቶለት እስከ ምሽት እስከ 4 ሰዓት እንድንጫወት አስችሎናል ይላል። ወጣት ዳዊት ደማሙና አቤል ነጋሲ በበኩላቸው፤ የስፖርት ማዘውተሪያው የምሽት አገልግሎት መስጠት መጀመር ቀን ስራ ውለን ማታ ጊዜያችንን በስፖርት እንቅስቃሴ እንድናሳልፍ አድርጎናል ብለዋል። ይህም ከአብሮ አደግ ጓደኞቻችን ጋር ያለን ኅብረት እንድናጎለብት አስችሎናል ይላሉ። በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት የሚገኘው የስፖርት ማዘውተሪያም በምሽት አገልግሎት እየሰጠ ነው። በዚሁ ወቅት ወጣት ተከተል ታዬ እንዳለው፤ ሜዳው ከዚህ ቀደም በአካባቢው ያልነበረና የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ የተገነባ ነው። በተለይም በምሽት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሰረተ ልማቶች መያዙ ማታ ከስራ መልስ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ጤናችን እንድንጠበቅ እያስቻለን ነው ብሏል። በዚህም ከእኩዮቹ ጋር ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት የጤና ቡድን መስርተው እየሰሩ መሆናቸውን ገልጿል። የስፖርት ማዘውተሪያው አገልግሎት ከረዥም ጊዜ በኋላ ወደ ስፖርት እንድመለስ አድርጎኛል በማለት የገለጸው ደግሞ ወጣት ማይክ ብርሃኔ ነው። የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አሰግደው ኃይለጊዮርጊስ፤ በመዲናዋ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች የስፖርት ማዘውተሪያ እጥረት ከመቅረፍ ባሻገር ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የከተማዋ ወጣቶችም አልባሌ ቦታ እንዳይውሉና ጤናቸውን እንዲጠብቁ በማድረግ በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ የስፖርት ማዘውተሪያዎቹ የምሽት አገልግሎት መስጠት መጀመራቸው በተለይም ነዋሪዎች ከስራ መልስ ምቹ በሆነ ሜዳ ላይ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት ቦታ መኖሩ በርካታ ጥቅሞችን እያስገኘ ነው ብለዋል። በቀጣይም የስፖርት ማዘውተሪያና መዝናኛዎችን የማስፋፋት እንዲሁም የወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላትን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አካባቢ ጥበቃ
ለቀጣዩ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የችግኝ ዝግጅት እየተከናወነ ነው
Mar 27, 2026 66
ሆሳዕና፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ ሻራ መርሐ-ግብር የችግኝ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ አስታውቋል። የቢሮው ኃላፊ አብርሃም መጫ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ባለፉት 7 ዓመታት በክልሉ 450 ሺህ ሔክታር በአካባቢ ጥበቃና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ማልማት ተችሏል። በዚህም የአፈር ለምነትን በማስጠበቅ፣ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥን ጨምሮ በበርካታ ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አብራርተዋል። በዚህ ዓመትም 270 ሚሊየን የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል 80 ሺህ ሔክታር መሬትን ለማልማት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራን ነው ብለዋል። ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ ለምግብነትና ለሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የሚውሉ ችግኞችን የማፍላትና የማዘጋጀቱ ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝም ነው ያረጋገጡት።
የበልግ ዝናብ ስርጭት ለግብርና ምርታማነትና ለእንስሳት መኖ አቅርቦት ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ነው-የኢትዮጵያ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
Mar 26, 2026 195
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018(ኢዜአ)፦የዘንድሮው የበልግ ዝናብ ስርጭት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ለሚከናወኑ የግብርና ስራዎች ስኬታማነትና ለእንስሳት መኖ አቅርቦት መሻሻል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር የኢትዮጵያ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ የትንበያ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አሳምነው ተሾመ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ ተቋሙ የአየር ጸባይ አዝማሚያዎችን፣አዎንታዊና አሉታዊ ተጽዕኖዎችን በወቅቱ ለማህበረሰቡና ለሚመለከታቸው ተቋማት የማድረስ ስራውን በልዩ ትኩረት እየከወነ ይገኛል። ከየካቲት እስከ ግንቦት ባለው የበልግ ወቅትም፣ በተለይም በሀገሪቱ ደቡባዊ አጋማሽ የዓመታዊ ዝናብ መጠኑ እስከ 55 በመቶ የሚሸፈንበት ዋነኛ ወቅት ነው ብለዋል። በ2018 ዓ.ም የበልግ ወቅት አብዛኞቹ የአገሪቱ አካባቢዎች መደበኛና ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ እንደሚያገኙ ተናግረዋል፡፡ እስካሁንም በ55 የሚደርሱ አካባቢዎች በ24 ሰዓት ውስጥ ከ35 እስከ 148 ሚሊ ሜትር የሚደርስ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ መመዝገቡን ገልጸዋል። ባለፉት ቀናት የታየው ተስፋ ሰጪ የዝናብ ስርጭት ለአርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት ጠቅሰው፥ ለበልግ እርሻ ዝግጅትና ለዘር ስራ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩንም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ለሰውና ለእንስሳት የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን ማሻሻሉን እንዲሁም የእንስሳት መኖ ልማትን በማፋጠን ረገድ ከፍተኛ ድርሻ መኖሩ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። በመጪዎቹ ሚያዝያና ግንቦት ወራትም በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብ፣ በመካከለኛውና በሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች የበልግ ዝናብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በተለይም በደቡብና በደቡብ ምዕራብ አካባቢዎች ዝናቡ ዘግይቶ የሚወጣ በመሆኑ ለግብርናውና ለአካባቢ ጥበቃ ስራው ተጨማሪ ዕድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል። ይሁን እንጂ፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ወደ ጎርፍ አደጋ ሊቀየር ስለሚችል ማህበረሰቡና የሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል።
በጣና ሐይቅ ላይ እየተስፋፋ የመጣውን የእምቦጭ አረም ለማጥፋት አዲስ የንቅናቄ ዘመቻ ተጀመረ
Mar 25, 2026 106
ባህር ዳር ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ በጣና ሐይቅ ላይ እየተስፋፋ የመጣውን የእምቦጭ አረም ለማጥፋት አዲስ የንቅናቄ ዘመቻ ተጀመረ። የአማራ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በሐይቁ ህልውና ላይ አደጋ የደቀነውን የእምቦጭ አረም በተደመረ አቅም ለማስወገድ የትብብር ጥሪ አቅርቧል። ከጣና ሃይቅና አካባቢው የእምቦጭ አረምን ለማስወገድ የሚያስችል የንቅናቄ መርሃ ግብር በባህር ዳር ከተማ ሽንብጥ ቀበሌ የጣና ዳርቻ በዛሬው እለት በይፋ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የአማራ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ሃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ፤ በጣና ሃይቅ ላይ እየተስፋፋ የመጣውን የእምቦጭ አረም በተባበረ ክንድ በማስወገድ የሃይቁን ህልውና መጠበቅ ይገባናል ብለዋል። አረሙን ለማጥፋት በሰው ኃይል እና በማሽን እንዲሁም አጠቃላይ የሕዝቡን ጠንካራ ተሳትፎ ማእከል ያደረገ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል። የእምቦጭ አረም በቀላሉ የመስፋፋትና የማንሰራራት ባሕሪ ያለው በመሆኑ ቀጣይነት ያለው ዘመቻ እና የክትትል ስራ የሚያስፈልግ ስለመሆኑም አፅኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም በሐይቁ ህልውና ላይ አደጋ የደቀነውን የእምቦጭ አረም በተደመረ አቅም ለማስወገድ እንዘጋጅ በማለት ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል። የመከላከል ሥራው በሰው ኃይልና በማሽነሪ በመታገዝ እንዲሁም ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በባዮሎጂካል ዘዴ እየተከናወነ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የተያዘውን ሀገራዊ ግብ ማሳካት በሚያስችል መልኩ ዝግጅት እየተደረገ ነው
Mar 25, 2026 111
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ በ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የተያዘውን ሀገራዊ ግብ ማሳካት በሚያስችል መልኩ ውጤታማ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የአረንጓዴ አሻራ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ(ዶ/ር) ገለጹ። አስተባባሪው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ዘንድሮ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር፣ የመጀመርያው ምዕራፍ ማጠቃለያ ዓመት በመሆኑ ዝግጅቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዚህም በዘንድሮው መርሃ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ7 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ በላይ ለመትከል እቅድ ተይዞ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት የተገኙ ተሞክሮዎችን በማስፋት የፍራፍሬ ችግኞችን የማስፋት፣ የሀገር በቀል ዝርያዎችን ቁጥር ከፍ የማድረግ ብሎም የእፅዋት አይነት ስብጥር በሰፊው እየተሰራበት መሆኑንም ገልፀዋል። በበጋው ወቅት የተከላ ቦታዎችን የመለየት፣ የተለዩ ቦታዎች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ የማከናወን፣ ከየአካባቢው አየር ንብረት ጋር የሚጣጣሙ ችግኞችን የማፍላትና የተለዩ ቦታዎች ላይ ካርታ የማዘጋጀት ስራ በስፋት መከናወኑን ነው ያስታወቁት። በዚህም በክልሎች እስካሁን 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለችግኝ ተከላ የሚውሉ ቦታዎችን መለየታቸውን ጠቅሰው እስካሁን ከ110 ሺህ በላይ ችግኝ ጣቢያዎች ወደ ስራ ገብተው ችግኞች እያፈሉ ይገኛሉ ብለዋል። በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ7 ነጥብ 5 ቢሊየን በላይ ችግኝ ለመትከል በእቅድ መያዙን ተናግረው እስካሁን 6 ነጥብ 1 ቢሊየን ችግኝ ዝግጁ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በቀሪው ጊዜ የእንክብካቤ ተግባራት እንደሚከናወኑ ጠቅሰው ጉድጓድ የማዘጋጀት ስራዎችን ጨምሮ ሌሎችም እንደሚከናወኑ ገልጸዋል፡፡ ቀደም ሲል የነበረውን የክረምት ዝናብ ብቻ የመጠበቅ ልምድ መቀየሩን ጠቁመው ይህም ችግኞች ረጅም የዝናብ ወቅት እንዲያገኙ በማድረግ የፅድቀት መጠናቸውን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምረው አስረድተዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አሁን ላይ የህዝቡ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰው በቀጣይም የዜጎችን የባለቤትነት ስሜት የማሳደግ እና የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው
Mar 22, 2026 138
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
የኢጋድ እና ጃፓን ትብብር መጠናከር ለቀጣናዊ ሰላም የጎላ ሚና አለው
Mar 9, 2026 247
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ጃፓን በቀጣናው ሰላም ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሠሩ ገለጹ። የኢጋድ ምክትል ዋና ፀሐፊ መሐመድ አብዲ ዋሬ ከጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ዳይሬክተር ሂሮኒሪ ሱዙኪ ጋር በጅቡቲ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በኢጋድ ቀጣና ስላለው የሰላም እና ደኅንነት ሁኔታ ሐሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቀጣይም ትብብራቸውን በይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሠሩ ማረጋገጣቸውን ኢጋድ ሴክሬተሪያት መረጃ ጠቁሟል። ጃፓን ለኢጋድ እና አባል ሀገራት፤ በቀጣናው ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት መረጋገጥ ሥራ ዋና አጋር ሆና መቀጠሏም ተመላክቷል።
ሀገራት የሴቶች መብቶችን የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባቸዋል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Mar 9, 2026 256
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የሴቶች መብቶች እና የሥርዓተ ጾታ እኩልነነት የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን እንዲወስዱ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጥሪ አቀረቡ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። "መብቶች፣ ፍትሕ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሐሳብ ነው። የአፍሪካ ኀብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም፤ ቀኑ የአፍሪካ ሴቶች እና ልጃገረድ ስኬቶችን የምናከብርበት፣ ሴቶችን ማብቃት እና ጥበቃ ላይ የገባናቸውን ቃል ኪዳኖች ዳግም የምናድስበት ነው ብለዋል። ሴቶች በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ከአመራር ሰጪነት እስከ ቴክኒካዊ ቦታዎች ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም አመልክተዋል። የሥርዓተ ጾታ እኩልነት የተቋሙ ሥራ ማዕከል መሆኑንም አስረድተዋል። የአፍሪካ ኅብረትም ቀኑን እያከበረ ሲሆን፤ የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር በአፍሪካ የሴቶችን መብቶች የሚደግፉ ቁልፍ ማዕቀፎችን በዚሁ ወቅት አንስተዋል። ለአብነትም የአፍሪካ ኅብረት የሰው እና ዜጎች መብቶች ቻርተር የሴቶች መብቶች የሕግ ማዕቀፍ፣ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) እና የሴቶችና ልጃገረዶች ጥቃትን ማስቆም ያለመውን የኅብረቱ ን ኮንቬንሽን በማሳያነት ጠቅሰዋል። የኮንቬንሽኑ ወደ ትግበራ መግባት ትልቅ ስኬት እንደሆነ ገልጸው፤ ሀገራት በሕግ አውጪ ምክር ቤት ማዕቀፉን በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲያስገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ሊቀ መንበሩ የሥርዓተ ጾታ እኩልነት እና የልማት የትኩረት መስኮች ቁርኝት እንዳለውም አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የ2026 ትኩረት በሆነው ውኃ እና ንጽህና ጋር በተያያዘ፤ ሀገራት የሴቶችን ጫና የሚያቃልሉ እና ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን እንዲያከናውኑም ጥሪ አቅርበዋል።
በቀጣናው የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው -ኢጋድ
Mar 8, 2026 231
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂን ጨምሮ በቀጣናው የሴቶችን የአመራርና ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው። "መብቶች፣ ፍትህ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሴቶችን ቀን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፏል። ኢጋድ ለሴቶች አመራር ሰጪነት፣ አይበገሬነት እና በቀጣናው ሰላም፣ ብልጽግና እና ለውጥ ለማምጣት እያበረከቱት ላለው አስተዋጽኦ ክብር እና እውቅና እንደሚሰጥ ገልጿል። በኢጋድ ሴቶች በቀጣናው አመራር ሰጪነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የኢጋድ የሰላም፣ ግብርና፣ ዲጂታል ደህንነት፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና መሬት አስተዳደር ፎረሞች እንዲሁም የኢጋድ የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂ ጨምሮ የተለያዩ ኢንሼቲቮች እየተገበረ መሆኑን አመልክቷል። የሴቶች ድምጽ እንዲሰማ እና መሉ ተሳትፏቸው እንዲረጋገጥ የሚያግዙ መድረኮችን መፍጠሩን ነው የኢጋድ ሴክሬተሪያት በመረጃው ያስታወቀው።
ሐተታዎች
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3280
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 353
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 407
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 385
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ትንታኔዎች
ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት
Mar 26, 2026 102
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በኋላ የታዛቢነት (Observer) ደረጃን አገኝታለች። እ.ኤ.አ በ2006 የውጭ ንግድ ፖሊሲዋን የሚገልጽ ሰነድ ለድርጅቱ አቅርባለች። ሰነዱ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች፣ የወጪና ገቢ ንግድ ሕጎች፣ የቀረጥ፣ ከቀረጥ ውጭ ያሉ የንግድ ገደቦች፣ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ እና የኢንቨስትመንት ሕጎችን ያካተተ ነበር። በኢትዮጵያ እና በዓለም ንግድ ድርጅት መካከል የመጀመሪያው የድርድር ምዕራፍ የተጀመረው እ.አ.አ በ2008 ነው። ከእ.አ.አ 2008 እስከ 2012 በቆየው የቴክኒክ ድርድር ሶስት የስራ ቡድን ስብስባዎች ተካሂደዋል። በዚህ ወቅት የነበረው ድርድር በዋናነት ኢትዮጵያ ስለ ንግድ ሥርዓቷ ማብራሪያ የምትሰጥባቸው እንጂ፣ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘት አልቻሉም። ከእ.አ.አ 2012 እስከ 2019 የሁለቱ ወገኖች ድርድር ተቋርጦ ነበር፤ ለሰባት ዓመታት እንዲቋረጥ ያደረጉ የተለያዩ ምክንያቶች ይነሳሉ። በወቅቱ ስልጣን የነበረው የኢህአዴግ መንግስት "የገበያ ውድቀት" አለ ብሎ ያምን ነበር። ስለዚህም እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም እና ኢነርጂ ያሉ ስትራቴጂካዊ ዘርፎች በመንግስት እጅ መቆየት አለባቸው የሚል አቋም ነበረው። ይህ የመንግስት ጽንሰ ሀሳብ ድርጅቱ የተለያዩ ዘርፎች ለውጭ ክፍት መደረግ አለባቸው ከሚለው አቋም ጋር የሚጣጣም አልነበረም። በዓለም ንግድ ድርጅት የተጠየቁ የንግድ ስርዓትን የማዘመን ስራዎች በሚፈለገው መልኩ አለመሄዳቸውም ለድርድሩ መቆም እንደ ምክንያትነት ይነሳል። የለውጡ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ የአባልነት ድርድር በድጋሚ ነፍስ ዘርቷል። መንግስት በተለያዩ ዘርፎች የወሰዳቸው ጠንካራ የንግድ እና ኢኮኖሚ እርምጃዎች ድርድሩ በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀጥል አድርጓታል። መንግስት እንደ ቴሌኮም፣ ባንክ እና ሎጅቲክስ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉ በድርጅቱ እንደ ትልቅ ለውጥ የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያን ሕጎች ከድርጅቱ ህጎች ጋር የማጣጣም ስራም ተከናውኗል። ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለው የንግድ ሕግ ማሻሻያ ተደርጎበት ዘመናዊ የንግድ አይነቶች የተካተቱ ሲሆኑ፤ የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መቋቋም የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ላይ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል። ኢትዮጵያ የሸቀጦች ታሪፍ ቅናሽ ሰነዷን አሻሽላ አቅርባለች። ይህም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች የምትጥለው ቀረጥ በምን ያህል መጠንና በስንት ዓመት ውስጥ እንደሚቀንስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የገባችውን ቃል በተግባር ያሳየችበት ነው። በአሁኑ ሰዓት በዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ኢትዮጵያ በተናጠል እንደ ቻይና፣ ሩሲያ፣ አሜሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችና ካናዳ ካሉ ሀገራት እና ከአውሮፓ ህብረት ጋር የገበያ ተደራሽነት ድርድር እያደረገች ነው። በተደረጉት የተናጥል ድርድሮች ላይም ለኢትዮጵያ አባልነት ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። ከአዕምሯዊ ንብረት ጋር በተያያዘ የፈጠራ ውጤቶችን፣ የንግድ ምልክቶችን እና የባህል እሴቶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ ሕግና ተቋም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጓል። የጉምሩክ አሰራር የሸቀጦችን ፍሰት ለማሳለጥ የዲጂታል ጉምሩክ አሰራርን የማስፋፋት ስራ በመንግስት በኩል ተከናውኗል። 14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ስብስባ ከመጋቢት 17 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በካሜሮን ያውንዴ መካሄድ ጀምሯል። በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክም በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ያውንዴ ገብቷል። ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከስብስባው ጎን ለጎን የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን ሚኒስትሩ ከዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ (ዶ/ር) ጋር ያደረጉት ውይይትም በዋናነት የሚጠቀስ ነው። በውይይቱ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለድርጅቱ አባል አገራት ከ1200 በላይ ለሚሆኑ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠቷንና ከ419 በላይ የሕግና የፖሊሲ ይዘቶችን ማሳወቋን ጠቁመዋል። የያውንዴው ስብስባ ለኢትዮጵያ የአባልነት ጉዞ የፖለቲካ ድጋፍን ለማሰባሰብ ያስችላታል። በቅርቡ የድርጅቱ አባል ከሆኑ የአፍሪካ እና ሌሎች ሀገራት ጋር የቴክኒክ እና የተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግም ምቹ አጋጣሚ ይፈጥርላታል። የያውንዴው ውይይት ኢትዮጵያ በቴክኒክ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ ደረጃም ለድርድር ዝግጁ መሆኗን የምታሳይበት ነው። የዓለም የንግድ ድርጅት እ.አ.አ በ1995 የተቋቋመ ሲሆን ዋና መቀመጫው ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ነው።ድርጅቱ 166 አባል ሀገራት አሉት። አባል ሀገራቱ የዓለምን 98 በመቶ የንግድ ልውውጥን እንደሚሸፍኑ መረጃዎች ያመለክታሉ። የዓለም ንግድ ድርጅት በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው አቅምና ተጽዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው። ድርጅቱ ራሱ ገንዘብ የሚያበድር ባንክ ባይሆንም፣ የዓለምን የንግድ “የጨዋታ ሕግ" በመቅረጽ ረገድ ያለው ሚና ትልቅ መሆኑን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል መሆኗ የገበያ እድሏ እንዲሰፋ ያደርጋል። የኢትዮጵያ ምርቶች በ160+ አባል አገራት ገበያ ውስጥ ያለ አድሎና በዝቅተኛ ታሪፍ እንዲገቡ ዕድል ይሰጣል። ይህ በተለይም ለግብርና ውጤቶችና ለጨርቃጨርቅ ምርቶች ትልቅ በር ይከፍታል። የኢትዮጵያ አባል መሆን ሀገሪቷ ዓለም አቀፍ የንግድ ሕጎችን እንደምታከብር ማረጋገጫ ስለሚሆን፤ ትልልቅ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸው እምነት እንዲጨምር ያደርጋል። ኢትዮጵያ አባል መሆኗ ከሌሎች አገራት ጋር የንግድ አለመግባባቶች ቢገጥሟት፣ በድርጅቱ የክርክር መፍቻ መድረክ አማካኝነት መብቷን ማስከበር ትችላለች። ኢትዮጵያ የንግድ አቅሟን ለመገንባት የሚያግዙ ልዩ ልዩ ሥልጠናዎችንና የቴክኒክ ድጋፎችን ከድርጅቱ ማግኘት ትችላለች። ኢትዮጵያ በያዘችው ፍጥነት እና ቁርጠኝነት ከቀጠለች እ.አ.አ 2026 የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድሯን የማጠናቀቅ እድሏ ሰፊ ነው። የድርድሩ መጠናቀቅ ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማጽደቅ እና የአገር ውስጥ ህጎችን ከድርጅቱ ሕግ ጋር የማጣጣም ስራዎችን ጨምሮ በቀጣይ ምዕራፍ ለሚከናወኑ ስራዎች በር ይከፍታል። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን ውጥኗ ከ23 ዓመታት በኋላ እውን ሊሆን የተቃረበ ሲሆን ድርድሩም ወደ መደምደሚያው ምዕራፍ ደርሷል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 730
ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል የነዳጅ ብክነትን ለመቀነስ ምን ዓይነት ብልኀት መጠቀም ይመከራል? ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 21, 2026 205
በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ (በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት ስትወጥን የቀደመ ወረቷን፤ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶቿን ይዛ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን ቀረጸች። ይህን ዕውን ለማድረግ ስትዘይድም የሕዝቧን የፋይናንስ፣ የዕውቀት እና የጉልበት ዐቅም በመደመር መጠቀምን ሻተች። በዚህም መሠረት በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶችን አስመዘገበች። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። በኢዜአ ዐይን …! ✍️ ገበታ ለሸገር በአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻዎችና መናፈሻዎችን ለማልማት በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገው ገበታ ለሸገር ኢኒሼቲቭ፤ ከእንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ወንዝ ያለውን የሚሸፍን ነው። የሚሠራበትን ገንዘብ ለማሰባሰብም የገበታ ለሸገር የእራት ምሽት በዳግማዊ አጼ ምኒልክ የግብር አዳራሽ ተዘጋጀ፤ ባለሀብቶች፣ የንግድ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ጨምሮ ዓለም አቀፍና አኅጉራዊ ድርጅቶችም ተሳትፈዋል። ኢኒሼቲቩ አንድነት ፓርክን ጨምሮ የእንጦጦ መናፈሻንና ሌሎች የተለያዩ መዲናዋን ያስዋቡ በረከቶችን ችሯል። ይህም የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት በርካታ ቱሪስቶችን ከመሳብ ባለፈ፤ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለምጣኔ ሃብት ዕድገት ጉልኅ አስተዋጽዖ አበርክቷል። ለዚህ ሁሉ ስኬት መነሻ የሆኑትን ጉዳዮች ያስጀመሩትም ያስፈጸሙትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በገበታ ለሸገር የተገኙ ውጤቶችን መነሻ በማድረግ ገበታ ለሀገር የተሰኘውን ኢኒሼቲቭ አበሠሩ። ✍️ ገበታ ለሀገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነሐሴ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻን ለማልማት ያለመ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጅተዋል። ይህም በአዲስ አበባ ከተሠራው ገበታ ለሸገር ቀጥሎ የተከናወነ ነው። በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የገበታ ለሀገር ዓላማ የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ የቱሪስት መስኅብ የሚሆኑና የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ አካባቢዎችን ማዘጋጀት መሆኑን አስገንዝበዋል። በገበታ ለሀገር መርሐ-ግብር ባለሀብቶችን ጨምሮ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ 3 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህን ለማሳካት የሀገሪቱን ባለሃብቶች፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በተለያዩ መርሐ-ግብሮች የተሳተፉበት የገቢ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ውጤታማ ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገበታ ለሀገር ውጥን፤ እንደ ሀላላ ኬላ፣ ጨበራ ጩርጩራ፣ ወንጪ እና ጎርጎራ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና የተፈጥሮ ሀብቶችን አጉልተው በማሳየት ይበል ያሰኘ ውጤት አስመዝግቧል። ✍️ ገበታ ለትውልድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2015 ዓ.ም ገበታ ለትውልድ የተሰኘ ኢኒሼቲቭ ይፋ ያደረጉ ሲሆን፤ ይህም ተጨማሪ መዳረሻዎች እንዲለሙ አስችሏል። በዚህ ኢኒሼቲቭ ሥር በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች የመዳረሻ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል፤ እየተከናወኑም ነው። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዳሴ ግድብ አካባቢና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የፕሮጀክቱ አካል የሆኑ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራዎች እየለሙ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውን የሸበሌ ሪዞርት በይፋ መርቀዋል። እያንዳንዱ የሪዞርቱ ገጽታ የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ባህላዊ ሐብት የሚያንፀባርቅ ነው። ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በሚደረገው ጉዞ ትልቅ ታሪካዊ እጥፋት እንደሆነም ተገልጿል። ሎጎ ሐይቅ ሪዞርትም ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመረቀ ሲሆን፤ ለጎብኚዎች የማይረሳ ትውስታን የሚሰጥ እጅግ ማራኪ ቦታ ሆኖ ቀርቧል። ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለመሆን ያላትን ቁርጠኝነትና ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ቋሚ ምስክርም ነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት። የቱሪዝም ልማቱን ከተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ፣ ከዘላቂነትና ከአካታችነት ጋር በማቀናጀት፤ ሪዞርቱ የወሎ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ዕሴት ለዓለም ማኅበረሰብ የሚያስተዋውቅበት ሰፊ ገበታ ሆኖ ያገለግላል። ታሪካዊ ቦታዎችና የሀገር መገለጫ መሠረተ-ልማቶች ብሔራዊ ትርክቶችንም የሚገነቡ ናቸው። በአጠቃላይ እነዚህ ሁሉ ጥረቶች ለአካባቢ ጥበቃ ቅድሚያ በመስጠት ብሎም በየአካባቢው የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል። የቱሪዝም ዘርፉን ለማጎልበት፣ ብዙ ጎብኚዎችን ለመሳብ፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማጠናከር፣ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው። እንዲሁም ነባር ቅርሶችን በማደስና በመጠገን ለትውልድ ለማሻገር ደማቅ ዐሻራ አሳርፈዋል። በሌላ በኩል የቱሪዝም መዳረሻዎችን ማልማት የመንግሥት ብቻ እንዳልሆነ ዐሳይተዋል። ባለሀብቶችና ሌሎች የማኅበረሰብ ክፍሎችም ሀገራቸውን የመሥራት ሚና እንደሚጠበቅባቸው አሥተምረዋል። ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት ብሎም በርካታ የሥራ ዕድሎች በመፍጠር በኢኮኖሚው ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በኢትዮጵያም ቱሪዝም መንግሥት ላስጀመረው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የማዕዘን ድንጋይ ነው። ከአምስቱ ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎችም አንዱ የሆነው ለዚህ ነው። መሠረተ-ልማቶች ከሚገነቡባቸው ጡቦች ባለፈ የነገን ሀገራዊ ማንነት፣ ራዕይ እና መዳረሻን ይበይናሉ። ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ እንኳንም ታሰቡ፤ እንኳንም ተሳኩ። ይህ ባይሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ተጨማሪ መዳረሻ ባላገኘች ነበር።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 14, 2026 1411
ከየካቲት 29 - መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምሥራቅ ኢትዮጵያ • ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተመልክተዋል። ማዕከሉ በውስጡ 10 ተቋማት ይዞ 73 የሚሆኑ አገልግሎቶችን ለዜጎች እየሰጠ መሆኑንም ገልፀዋል። ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል • በተመሳሳይ በድሬዳዋ የተስማሚነት ምዘና ድርጅትን ጎብኝተዋል። ድርጅቱ ዓለም አቀፍ የአሠራር ሥርዓትን በመከተል ለአምራቾች፣ ለአገልግሎት ሰጪዎች፣ ለላኪዎች፣ ለአስመጪዎች፣ ለተቆጣጣሪ መሥሪያ ቤቶች፣ ለምርምር ተቋማትና ለሸማቹ ማኅበረሰብ የምርትና አገልግሎቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ተናግረዋል። • የድሬዳዋ የኮሪደር ልማትንም የጎበኙ ሲሆን፤ የኮሪደር ልማቱ ምቹ የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች፣ የተሻሻለ የአካባቢ ውበትን እና ጥራታቸውን የጠበቁ የማኅበረሰብ መሰብሰቢያ ስፍራዎች በድሬዳዋ ዕውን እንዲሆኑ ማስቻሉን አስረድተዋል። • ከድሬዳዋ ነዋሪዎች ጋርም የረመዳን ኢፍጣር መርሐ-ግብር ያከናወኑት ባለፈው ሳምንት ነው። • በድሬዳዋ የሚገኘውን እመርታ ቤተ-መጻሕፍትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎብኝተዋል። ቤተ-መጻሕፍቱ በአንድ ጊዜ ለ1 ሺህ ሰው አገልግሎት መስጠት እንደሚችል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። • በሳምንቱ መጀመሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሐረሪ ክልል ሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተሠራውን የገጠር ኮሪደር ሥራ ተመልክተዋል። የአካባቢው ነዋሪ በንቃት የተሳተፈበት የገጠር ኮሪደር ሥራ፤ ባሕላዊ የግንባታ ዘዴን፣ የተደራጀ ዕቅድ እና ተግባራዊ የአሠራር ውጤት ያሳየ መሆኑን አብራርተዋል። • የቁንድዶ ተራሮችንም ጎብኝተዋል። • በሐረር ከተማ የተቋቋመውን መሶብ የአንድ ማዕከልም ተመልክተዋል። ማዕከሉ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል አቀናጅቶ የማቅረብ ሀገር ዐቀፍ መርሐ-ግብር አካል መሆኑንም አስገንዝበዋል። • በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ በሎ ወረዳ የሚገኘውን ናሲኦል ዋሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት ጎብኝተዋል። • ከሐረር ከተማ ነዋሪዎች ጋርም የረመዳን ኢፍጣር አካሂደዋል። ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሹመት መስጠታቸው • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ ሌ/ጄኔራል አሥራት ደኔሮን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር፣ ረዳት ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድን እና አቶ ኤርዚቅ ኢሳን የአዲስ አበባ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነሮች አድርገው የሾሙት ባሳለፍነው ሳምንት ነው። ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከልዑካቸው ጋር በጅቡቲ የቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሐመድ እና የጅቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ዑማር ጊሌ በተገኙበት ውይይት አድርገዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥራ ጉብኝታቸውን ቀጥለውም ወደ ተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በዚሁ ወቅትም ከፕሬዚዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተወያይተዋል። ውይይታቸውም በሀገራቱ መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብር እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር። ✍️ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ከዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ኅብረት ጋር መምከራቸው • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ባዘጋጀው የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይ ታድመዋል። በዚሁ ወቅትም የሁሉም እምነት፣ ባህልና ሥርዓት የሚከበርባት ኢትዮጵያን መገንባት የመደመር መንግሥት ተልዕኮ መሆኑን ገልጸዋል። • ከዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ኅብረት ዳይሬክተር ኮስማስ ዛቫዛቫ (ዶ/ር) ጋር በዲጂታል ልማት ያለ ትብብርን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት ያደረጉት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በቀጣይም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ከግብ ለማድረስ እና ትብብራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር በጀመርናቸው እና በሌሎች አዳዲስ ዘርፎች ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ተስማምተናል ሲሉም ገልጸዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። • በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አዘጋጅነት በተከናወነው የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይም የታደሙ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት “ጎረቤቱ ርቦት እርሱ ጠግቦ የሚያድር ከኛ አይደለም” የሚለው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) አስተምኅሮ፣ ለሰው ልጅ ክብር መስጠትን፣ ርኅራኄን፣ የጋራ ደስታንና አብሮነትን በተግባር መተርጎም እንዳለብን የሚያሳይ ኅያው የሕይወት ስንቅ ነው ብለዋል። ✍️ የመሬት ናዳና ጎርፍ አደጋ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ • ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በተከሰተ የመሬት ናዳ እና ጎርፍ የዜጎች ሕይወት አልፏል፤ በንብረት ላይም ውድመት ደርሷል። ይህን ተከትሎም ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች የሐዘን መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል። • ከዚሁ ጋር በተያያዘ በጋሞ ዞን በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም ከፌደራል መንግሥት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ ያስታወቁት ባሳለፍነው ሳምንት ነው። እስካሁንም በአደጋው ሳቢያ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስና መልሶ ለማቋቋም ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ በተቀናጀ መንገድ እየተሠራ መሆኑን አረጋግጠዋል። መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ለወገኑ ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ✍ ምክር ቤቱ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ማወጁ • የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት ምክንያት ሕይወታቸው ያለፉትን ዜጎች በማስመልከት ብሔራዊ የሐዘን ቀን ዐውጇል። በዚህም መሠረት ትናንት የጀመረው ብሔራዊ የሐዘን ቀኑ እስከ ነገ ድረስ የሚቆይ ይሆናል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ዐበይት_ጉዳዮች #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3745
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2518
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8309
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6794
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ተከፍሎ የማያልቅ የኢትዮጵያ እና ሕዝቧ ውለታ አለብን - የመናዊያን ፍልሰተኞች
Mar 19, 2026 2353
በዮሐንስ ደርበው ምድረ ቀደምቷ ሀገር ኢትዮጵያ ለተገፉ፣ ጥላ ከለላ ለሚሹ፣ ለተከዙና ለታረዙ የሀገራት ዜጎች መጠጊያ ናት። የኢትዮጵያን ቸርነትም ከተጠለሉባት እንግዶቿ በላይ ምሥክር የለም። የኢትዮጵያን ደጅ የረገጡ ሁሉ በቆይታቸው ለተደረገላቸው ሁሉ ‘ውለታችንን በምን እንክፈል’ ሲሉ ይደመጣሉ። ከአያሌ ሀገራት በመልከ ብዙ ቀውሶች ሳቢያ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሁሉ የቆሰሉ ልባቸው ታክሞ፣ ዕንባቸው ታብሶና ሕይወታቸው ታድሶ ኑራቸውን አደላድለዋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በዚህም ከአፍሪካም ሆነ ከተቀረው ክፍላተ ዓለም የጦርነትና ግጭት ጥላ ያጠላባቸውና ሰላምን የተጠሙ የቀጣናው ሀገራት ዜጎች ኢትዮጵያን ሲሹ ማየት የተለመደ ነው። የየመን ዜጎች ለዚህ ማሳያ ናቸው። ኢብቲሳም ኻሊድ እና መሰል የመናዊያን ከየመን የእርስ በርስ ግጭት በኋላ የኢትዮጵያን ደጅ ረግጠው ዛሬ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሚተርፍ የተድላ ኑሮ እየኖሩ ነው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረገችው ኢብቲሳም እንደምትለው፤ በየመን አለመረጋጋት በፈጠረው ጠባሳ እርሷና መሰሎቿ ለፍልሰት ተዳርገዋል። ለዚህ ደግሞ ምርጫቸው ኢትዮጵያ ሆነች። ወደ ኢትዮጵያም መጥተው የሀገሬው ፊት ሳይኮሰኩሳቸው በፍቅር እንደተቀበሏቸው ትናገራለች። በዚህም ዛሬ የመናዊያን ተስፋቸው ለምልሞ፣ ሕይወታቸው ሠምሮ ኢትዮጵያን እንደ እናት ቆጥረው እየኖሩ ስለመሆኑ ትናገራለች። ከ11 ዓመታት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የመጣችው ኢብቲሳም፤ በወቅቱ ቀኑ እንደጨለመባት ታወሳለች። ሰው ከቤቱ፣ ከወገኑ…ከሀገሩ ወጥቶ ወዴት ይሄዳል? በወቅቱ የነበረውን ጭንቀት ማየልም ታስታውሳለች። አሁን ግን ስለ ኢትዮጵያ እና ሕዝቧ በጎነት ዐውርታ አትጠግብም። “አሁን ፍልሰተኛ አይደለሁም፤ ያለሁት በሁለተኛዋ ሀገሬ ኢትዮጵያ ነውና” ትላለች። እንዲህ ባለው የረመዳን ወቅት ደግሞ የፍልሰተኞች ሁሉ ሰብሳቢ ናት። “ሁሉም ከእነ ቤተሰቡ ወደ ቤቷ እየመጣ ያፈጥራል። በዚህም በፍልሰት እንደመጡ ሳይሆን ቤተሰባዊነት ይሰማቸዋል። ከየመን፣ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ኤርትራ፣ አፍጋኒስታን፣ ኮንጎሊዝ (DRC) ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሁሉ ሰብሰብ ብለው የኢፍጣር መርሐ-ግብርን እንደሚያከናውኑም ታነሳለች። በዚህ ላይ ኢትዮጵያውያን ብርታት ናቸው ትላለች፤ ሁሌም ‘አይዟችሁ፣ በርቱ፣ ነገ ጥሩ ይሆናል’ እያሉ ያበረቱናል፤ ክብርና ፍቅር ይሰጡናል ስትልም ታስረዳለች። የኢትዮጵያንና ሕዝቧን ውለታ እንዴት መክፈል ይቻላል? ኢትዮጵያን ሀገራችን ብለን ነው እየጠራን ያለነው። እንደ እንግዳ እንደ ፍልሰተኛ እራሳችንን አናስብም፤ እንደሀገሬው አንዱ እንጅ፤ የምትለው ኢብቲሳም፤ ኢትዮጵያን እንዴት ብዬ ነው የምገልጻት? እናትን መግለጽ ይቻላል? እናትን መግለጽ ከተቻለ ኢትዮጵያን በዚያ ልክ መግለጽ ይቻል ይሆናል፤ እኔ ግን አይቻለኝም በማለት ትናገራለች። “የዛሬ 11 ዓመት ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት፤ የሰው ፊት አልገረፈኝም፤ ፊቱን ያዞረብኝም የለም። ኢትዮጵያውያን ደግ፣ ቅንና ደስ የምትሉ ሕዝቦች ናችሁ” ስትል ስሜቷን ትገልጻለች። ኢትዮጵያ እንደ ኒውዮርክ እያደገች ነው፤ እኛ ከመጣን በኋላ እንኳን በርካታ ለውጦች ዕያየን ነው ስትልም የኢትዮጵያን የለውጥ ሂደት አንስታለች። ለአብነትም ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በርካታ ነገሮች መስተካከላቸውን በመጠቆም፤ ለዚህም የኢትዮጵያን መንግሥት እናመሠግናለን ብላለች። ከፍልሰተኞች ጋር በተያያዘ በርካታ ሕጎች በመሻሻላቸው፤ ዛሬ በራሴ ስም ንግድ ፈቃድ አውጥቼ እየሠራሁ ነው፤ በጨረታዎችም እወዳደራለሁ፤ የበጎ አድራጎት ማኅበር መመሥረትና መምራት ችያለሁ። እነዚህ ሁሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ያመጣቸው ለውጦች ናቸው ብላለች። በምድረ ኢትዮጵያ ያለን ሁሉ ለኢትዮጵያ ዕድገት እንተባበር ስትልም ጥሪ አቅርባለች። ህልማችን ከኢትዮጵያውያን ጎን ሆነን ኢትዮጵያን በማሳደግ ጥረት በንቃት መሳተፍ ነው፤ የኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ውለታ መመለስ አለብን ስትልም ትናገራለች። በኢብቲሳም ኻሊድ ቤት በተዘጋጀ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይ የተሳተፈው አነስ አንዋር ለኢዜአ እንዳለው፤ ኢትዮጵያ በሯን ከፍታ አስጠልላዋለች። ከተለያዩ ሀገራት ብንመጣም ሰብሰብ ብለን ስናፈጥር፤ ማኅበራዊና ቤተሰባዊነታችን ይጠናክራል ብሏል። ብዙ ፈተናዎችን ዐይተናል፤ አልፈናቸው እዚህ ደርሰናል የሚለው አነስ፤ “ኢትዮጵያዊነት መልካምነት ነው” ሕዝቡ በክብር ነው የተቀበለን፤ ከምሥጋና ውጭ ምን ማለት እንችላለን? አመሥጋኞች ነን ሲል ገልጿል። እየተማርኩ ነው፤ ትምህርቴን አጠናቅቄ በሙያዬ በመሠማራት ኢትዮጵያን ማገዝ እፈልጋለሁ ብሏል። ራኪያ አሊ አብዱረዛቅ በበኩሏ በፈረንጆቹ 2011 ወደ ኢትዮጵያ መምጣቷን ታወሳለች። ትምህርቷንም ተከታትላ መመረቋን ገልጻ፤ ቤተሰብ አፍርታ ሁለት ልጆችንም ወልዳ እየኖረች ነው። ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሀገሬ ናት፤ ሰላም አላት፤ ሕዝቡም ሰው አክባሪ ነው። ለኢትዮጵያ የተሻለ ልማት ደግሞ መተባበር ወሳኝ ስለሆነ ለዚሁ እንትጋ ስትል መልዕክቷን አስተላልፋለች። #ፍልሰተኞች #ኢዜአ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 672
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡