ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የወጣቶች አደረጃጀቶች በበጎ ፍቃድ ደም ከመለገስ ባሻገር የማህበረሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ላይ ተሳትፎአቸውን እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ
Dec 14, 2025 23
አዳማ፤ ታህሳስ 5/2018(ኢዜአ)፡-የወጣት አደረጃጀቶች በበጎ ፍቃድ ደም ከመለገስ ባሻገር የማህበረሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ላይ ተሳትፎአቸውን እንዲያጠናክሩ የኢትዮጵያ ደምና ሕብረህዋስ አገልግሎት ጠየቀ። አገልግሎቱ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ደም ለጋሽ ማህበር ጋር ባለፉት አምስት ወራት ያከናወናቸውን የደም አሰባሰብ ሂደትና የቀጣይ በጋ ወራት የደም አሰባሰብ ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዳማ አካሄደዋል ። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አሸናፊ ታዘበው እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ 550 ሺህ ዩኒቲ ደም ለመሰብሰብ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን ጨምሮ ተማሪዎች፣ የኃይማኖት ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው። ለተግባራዊነቱም የማህበረሰቡን የደም የመለገስ ባህል ለማሳደግ የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶችና ትምህርት ቤቶች በማሳተፍ ባለፉት አምስት ወራት 202 ሺህ ዩኒቲ ደም ተሰብስቧል ብለዋል። የበጎ ፈቃድ ስራውን በበጋ ወራት ለማስቀጠል የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶች ከሚያደርጉት የበጎ ፍቃድ የደም ልገሳ ባሻገር ህብረተሰቡን በማስገንዘብ ረገድ ያላቸውን ሚና እንዲያጠናክሩ መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። አገልግሎቱ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ጂማ እና ጂግጅጋን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች ቋሚ ደምለጋሽ አባላት ማፍራቱን አንስተዋል። ወጣቶቹ በበጎ ፈቃድ በሚለግሱት ደም ሌሎች እንዲሳተፉ የንቅናቄ ተግባር ላይ በመሳተፍ ህይወት እያዳኑ ነው ብለዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ሙሉጌታ እንዳለ በበኩላቸው የመዲናዋን የጤና ተቋማት የደም ፍላጎት ለማሟላት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በደም እጦት ምክንያት የሚሞቱ እናቶችና ዜጎችን ቁጥር ዜሮ ማድረግ እንደተቻለ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ደም ለጋሽ ማህበር አስተባባሪ ወጣት ነቢዩ ሙሰማ በበኩሉ ማህበሩ በደም እጦት የሚሞቱ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ አባላቱን በማስተባበር ደም እያሰባሰበ ይገኛል ብለዋል። ማህበሩ በየሶስት ወሩ በቋሚነት ከሚሰበሰበው ደም በተጨማሪ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ደም እንዲለግሱ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ባለፉት አምስት ወራት ማህበሩ ሲያከናውን የቆየውን የደም ልገሳ በበጋ ወራት ለማጠናከር ማቀዱን ጠቁመዋል።
በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በመሰማራት ተኪ ምርት ላይ በማተኮራችን ውጤታማ ሆነናል-ማህበራት
Dec 14, 2025 39
ወልቂጤ፤ታህሳስ 5/2018 (ኢዜአ):-በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በመሰማራት ተኪ ምርት ላይ በማተኮራቸው ውጤታማ መሆናቸውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዘርፉ የተሰማሩ ማህበራት ተናገሩ። የክልሉ ስራ እድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ በበኩሉ በተለያዩ የስራ ዘርፎች የሚሰማሩ ዜጎች ውጤታማ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፆ፥በተያዘው ዓመት ለ400 ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጠር ይሆናል ብሏል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተደራጁ ማህበራት በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ተኪ ምርቶችን በማምረት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በሆሳዕና ከተማ የሚገኘው የዋቻሞ ኢንተርፕራይዝ ተወካይ ወይዘሪት ምስጋና ዝግዴ ከዓመት በፊት ለ5 ተደራጅተው ቡና በዘመናዊ ማሽን በመፍጨትና ቆልቶ በማሸግ ስራ ላይ መሰማራታቸውን ተናግራለች። መንግስት ወደዚህ ስራ እንዲገቡ ክህሎታቸውን ከማሳደግ ባለፈ የመስሪያ ቦታ እንዳመቻቸላቸው ገልፃ፥ የቡና ምርቱን ከሃገር አልፎ ወደ ውጭ በመላክ የገበያ ትስስራቸው መስፋቱን አንስታለች። በመቶ ሺህ ብር የጀመሩት ካፒታል አሁን ላይ ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ መድረሱን ገልጻ፥በዚህም ኢኮኖሚያቸውን በማሳደግ ለ30 ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግራለች። በቡታጅራ ከተማ የሚገኘው የአግኖት የሳሙናና እና ዲተርጀንት ማምረቻ ማህበር ሰብሳቢ ወይዘሮ አይዳ ወልጫፎ በበኩላቸው፥ ሶስት ሆነው የጀመሩት ስራ ውጤታማ ሆኖ ምርታቸውን ለገበያ ማቅረብ መጀመራቸውን ገልጸዋል። ምርቱን ለማምረት ሁሉም ግብአቶች በሃገር ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን ገልጸው፥በዚህም ከውጭ ይገቡ የነበሩ ሳሙናና የንፅህና መጠበቂያ ዲተርጀንቶችን በሃገር ውስጥ ማምረት መቻላቸውን ተናግረዋል። የተፈጠረው የገበያ ትስስር ውጤታማ እንዳደረጋቸው እና በስፋት ለመስራት እያነሳሳቸው መሆኑን አመልክተዋል። መንግስት የመነሻ ብድርና የመስሪያ ቦታ እንዲሁም የሊዝ ማሽን በማቅረቡ ወደ ስራ መግባታቸውን የገለፁት ደግሞ በክልሉ በመስቃን ወረዳ በቤትና በቢሮ ዕቃዎች ምርት ላይ የተሰማሩት አቶ ማረኝ ደመቀ ናቸው። በዚህም ከውጭ ይገቡ የነበሩ የቤትና የቢሮ መገልገያ የእንጨት ውጤቶችን በማምረት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ፥ በክልሉ ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት በማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ውጤት እየተገኘ ነው ብለዋል፡፡ ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ በማድረግ የተገኘውን ውጤት የማስቀጠል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፥ ዘርፉ ለበርካቶች የስራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ለ400 ሺህ ስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጠር የገለጹት አቶ ሙስጠፋ፥ ባለፉት ወራት ውስጥ ከ193 ሺህ 104 ዜጎች በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፈጠሩን ገልፀዋል። የክህሎት ስልጠና፣የገበያ ትስስር መፍጠር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታዎችን ማመቻቸት እንዲሁም ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበት ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል እና አገልግሎቶቹን የማስፋት ሥራ እየተከናወነ ነው
Dec 14, 2025 35
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 5/2018(ኢዜአ)፡- መሶብ የአንድ ማዕከልንና የሚሰጡ የአገልግሎት ዓይነቶችን ለማስፋት እየተሠራ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሠመረ ጂራታ(ኢ/ር) ተናገሩ። ለዜጎች የሚሰጥ አገልግሎት ከቅሬታ የጸዳ፣ ጊዜና ወጭ ቆጣቢ፣ ፍትሐዊ ብሎም ተደራሽ እንዲሆን ማስቻል የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዓላማ መሆኑን አስገንዝበዋል። እንደ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአምሥት የክልል እና በሦስት የፌደራል ተቋማት በ33 ዘርፎች አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። እስካሁንም ከ6ሺህ 300 በላይ ተገልጋዮች አገልግሎት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል። በቀጣይ ወደ ማዕከሉ የሚገቡ ተቋማትና አገልግሎቶችን ቁጥር የማስፋት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህም መሠረት ተጨማሪ አንድ የፌደራል እና ሦስት የክልል ተቋማት ወደ መሶብ የአንድ ማዕከል መግባት የሚያስችላቸውን ሥራ እያከናወኑ ነው ብለዋል። ይህን ተከትሎም በአጭር ጊዜ አምሥት ተጨማሪ አገልግሎቶች ወደ ማዕከሉ እንደሚገቡ አመላክተዋል። በሌላ በኩል በአሶሳ ከተማ አሥተዳደር ደረጃ መሶብ የአንድ ማዕከል እንዲኖር እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ለቡና ልማት፣ ጥራትና ግብይት የተሰጠው ትኩረት አምራቹን ተጠቃሚ በማድረግ ለሀገርም የውጭ ምንዛሪ ገቢ እያሳደገ ነው
Dec 14, 2025 48
አዶላ፤ ታህሳስ 5.2018(ኢዜአ) ፡- ለቡና ልማት፣ ጥራትና ግብይት የሰጠው ትኩረት አምራቹን ተጠቃሚ በማድረግ ለሀገርም የውጪ ምንዛሪ ገቢ እያሳደገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ገለጸ። በጉጂ ዞን አዶላ ወዩ ዙሪያ ወረዳ ቢርቢርሳ ቢሉ ቀበሌ የተቋቋመው የቡና ጣዕም ቅምሻ ማዕከል የፌዴራል እና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር)፣ ባለፉት ዓመታት መንግስት ለቡና ልማት፣ ጥራትና ግብይት የሰጠው ትኩረት አምራቹን ተጠቃሚ እያደረገ ለሀገርም የውጭ ምንዛሪ ገቢ እያሳደገ መምጣቱን ተናግረዋል። በተለይም በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሻሻሉ የቡና ችግኝ ዝርያን በመጠቀም የቡና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች በተከታታይ ሲሰሩ ቆይተዋል ብለዋል። የቡና ምርትን በጥራት ለማሳደግ አምራች አርሶ አደሮችን፣ ነጋዴዎችንና ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የግንዛቤ ማሳደግ ስራዎች በሁሉም አካባቢዎች መሰራቱን አውስተዋል። በዚህም መሰረት ባለፈው ዓመት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የቀረበ የቡና ምርት ማሳደግ መቻሉን ገልጸው፤ ዘንድሮም የተሻለ ምርት እንደሚሰበሰብ ይጠበቃል ብለዋል። የኦሮሚያ ክልልም የቡና ምርት በስፋት ከሚሰበስብባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ትልቁ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም የጉጂ ቡና በተፈጥሮ ጣዕምና ጥራቱ ከሀገር አልፎ በአለም ገበያ ይበልጥ አዋጭ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። በዞኑ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የቡና ጣዕም መቅመሻ ማዕከልም በአካባቢው የሚመመረተው ቡና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለገበያ እንዲቀርብ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው አመልክተዋል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ፣ በክልሉ የቡና ምርታማነትን የማሳደግ እና ጥራትን የማስጠበቅ ስራዎች ውጤታማ እየሆኑ መጥተዋል ብለዋል። ከክልሉ ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ ምርት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የቡና ጣዕም ቅምሻ ማዕከሉ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል። የጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ነጋሽ ቡላላ በበኩላቸው ከዞኑ ባለፈው ዓመት ከ70 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን አስታውሰዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም ከዞኑ ከ120 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን ጠቅሰው፤ በዞኑ ከ160 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች የቡና ልማት ተሳታፊና ተጠቃሚእንደሆኑና ከ473 ሺህ ሄክታር በላይ በቡና ሊለማ የሚችል ሰፊ መሬት መኖሩን አመላክተዋል፡፡ በዞኑ የተቋቋመው የቡና ጥራትና ጣዕም ቅምሻ ማዕከል አምራቹን ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ በዞኑ አዶላ ሬዴ ወረዳ የአንፈራራ ቀበሌ ቡና አምራች አቶ ታሪኩ መራሚ፣ ማዕከሉ ቡናን ይበልጥ በጥራት ለማልማት የሚያበረታታ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ልማቱን በማስፋፋት ሰርተን ለመለዋጥ ብሎም ለሀገራችንም የውጭ ምንዛሪ ለማስገኘት ህግና ስርዓትን አክብረን እንድንሰራ ያደርጋል ብለዋል፡፡ ለተፈጥሮ ቡና ጣዕም ጥራትና ደረጃ መሻሻል ከማሳ ዝግጅት እስከ ምርት አሰባሰብ በግብርና ባለሙያዎች ሙያዊ ድጋፍ እያገኙ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በባሕርዳር ከተማ 24 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ
Dec 14, 2025 55
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 5/2018(ኢዜአ)፡- በባሕርዳር ከተማ ባለፉት አምስት ወራት 24 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 184 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሴ፤ የባሕርዳር ከተማን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል። ባለሃብቶች ወደ ከተማዋ መጥተው ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሳተፉ ባለፉት አምስት ወራት ጥረት ሲደረግ መቆየቱን አስረድተዋል። በዚህም 24 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 184 ባለሃብቶች አግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ሆቴልና ቱሪዝምን ጨምሮ በሌሎችም መስኮች ለመሰማራት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ጠይቀው እንደተሰጣቸው አስታወቀዋል። ባለሀብቶቹ ወደ ግንባታና ማምረት ስራ ሲሸጋገሩ ተኪና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ ለበርካታ ወገኖች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም ቀደም ሲል የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው በግንባታ ስራ ላይ ካሉ ፋብሪካዎች ባለፉት አምስት ወራት አምስቱ የማሽን ተከላ ስራቸውን አጠናቀው ወደማምረት ተግባር መግባታቸውን አንስተዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በማሽን ተከላ ስራ ላይ መሆናቸውን የጠቀሱት ኃላፊዋ፤ ፋብሪካዎቹ ፈጥነው የማሽን ተከላ ስራቸውን አጠናቀው ወደማምረት ስራ እንዲገቡ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። በማሽን ተከላ ላይ የሚገኙ ሁሉም ፋብሪካዎች ተጠናቀው ወደማምረት ተግባር ሲሸጋገሩ ተኪና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በብዛትና በጥራት ከማምረት ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እንዲፈጥሩና ለሀገሪቱ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አስተዋጽኦ በማበርከት ፋይዳቸው የጎላ ነው ብለዋል። በከተማዋ እስካሁን በማኒፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ 268 የተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች በማምረት ስራ ላይ እንደሚገኙ አውስተው፤ ኢንዱስትሪዎቹ በእንጨትና ብረታ ብረት፣ በምግብና ምግብ ነክ፣ በ" ጋርመንት እና ቴክስታይል " የስራ ዘርፎች የተሰማሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ከነዚህ ውስጥ 13 ኢንዱስትሪዎች ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርገው የተሰማሩ ሲሆን፤ በአጠቃላይ ከ11 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶችና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውን ከኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያው የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ፖለቲካ
በፀጥታና ደህንነት ተቋማት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ጉባዔዎችን በስኬት ለማስተናገድ አስችሏል
Dec 13, 2025 203
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦በፀጥታና ደህንነት ተቋማት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ዓለምአቀፍ እና አህጉራዊ ጉባዔዎች በስኬት እንዲስተናገዱ ማስቻሉን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ። የፀጥታና ደህንነት ተቋማት 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባዔ (ኮፕ- 32) በስኬት እንዲጠናቀቅ ከወዲሁ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑም ተገልጿል። "ጠንካራ የፀጥታና የደህንነት ተቋማት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ" በሚል መሪ ሃሳብ የፀጥታና የደህንነት ተቋማት የእውቅናና ምስጋና መርኃ ግብር እየተካሄደ ነው። መርኃ ግብሩ የተዘጋጀው በኢትዮጵያ የተዘጋጁ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ጉባኤዎችና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከበሩ ኃይማኖታዊና ህዝባዊ በዓላት በስኬት መጠናቀቃቸውን አስመልክቶ እንደሆነ ተገልጿል። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት በርካታ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ ጉባዔዎችን እንዲሁም ታላላቅ ሀገራዊ በዓላትን በታላቅ ስኬትና ሰላማዊ ሁኔታ ማስተናገድ ችላለች። እነዚህ ክስተቶች የሀገሪቷን የዲፕሎማሲ አቅም፣ የደህንነት ጥበቃ ብቃት እና ህዝባዊ ትብብር ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። በጸጥታና ደህንነት ተቋማት መካከል የነበረው ጠንካራ የመረጃ ልውውጥ ለስኬታማነቱ አይተኬ ሚና መጫወቱን አንስተዋል። በጉባዔዎቹ የእንግዶችን ደህንነት ከማረጋገጥ ባሻገር፣ በመዲናዋ የተረጋጋ ሁኔታን በመፍጠር ዲፕሎማሲያዊ ስራዎች ያለምንም እንቅፋት እንዲካሄዱ መደረጉን አመልክተዋል። ለዚህም በፀጥታና ደህንነት ተቋማት የተከናወኑት የሪፎርም ሥራዎች ዓለምአቀፍና አህጉራዊ ጉባዔዎችን በስኬት ለማስተናገድ አስችሏል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባዔን (ኮፕ- 32) እንድታስተናግድ መመረጧ ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን ገልፀው፤ ይህ ጉባዔ በስኬት እንዲጠናቀቅ የፀጥታና ደህንነት ተቋማት ከወዲሁ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም ለዓለም እና ለአፍሪካ ኢንተር ፖል ጉባዔም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የአፋር ክልል ህዝብ የፖለቲካ ተሳትፎና ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነቱ በተግባር እውን ሆኗል - የሰመራ ሎጊያ ነዋሪዎች
Dec 13, 2025 92
ሰመራ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የአፋር ክልል ህዝብ የፖለቲካ ተሳትፎና ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነቱ በተግባር እውን መሆኑን የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ በዛሬው ዕለት በሰመራ ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሄዷል። የመድረኩ ተሳታፊ የሰመራ ሎጊያ ነዋሪዎች ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የአፋር ክልል ህዝብ የፖለቲካ ተሳትፎና ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነቱ በተግባር እውን ሆኗል ብለዋል። በክልሉ የመስኖ ልማትን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ስራዎችም በስፋት እየተከናወኑ በመሆኑ ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የሚደረገው ጥረት እየተሳካ ስለመሆኑ አንስተዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ መሐመድ አብዱልቃድር በአፋር ክልል የተከናወኑና በመከናወን ላይ ያሉ የልማት ስራዎች ለሀገርም ጭምር የሚጠቅሙ ስለመሆናቸው ተናግረዋል። ከዚህ በፊት በነበረው የመንግስት አስተዳደር የክልሉ ህዝብ የፖለቲካ ተሳትፎና የልማት ተጠቃሚነት ፍትሃዊነት የጎደለው እንደነበር አንስተው በለውጡ እኩልነትና ፍትሃዊነት በተግባር ተረጋግጧል ብለዋል። በክልሉ ወጣቱን ማዕከል ያደረጉ የልማትና የስራ ዕድሎች እየተመቻቹ መሆኑን ያነሳው ወጣት አሊ ሰላል፤ በዚህ ረገድ ጅምሮች ቢሆኑም በቀጣይ ብዙ መሰራት እንዳለበት አንስቷል። በተለይም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርና ወንጀልን ለመከላከል ወጣቶችን በጥሩ ስነ ምግባር መቅረጽና በቂ የስራ እድል መፍጠር ይገባል ብሏል። የውይይት መድረኩን የመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)፤ በሁሉም አካባቢዎች የልማት ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል የሀገርን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ መንግስት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአፋር ክልል የተከናወኑ እና በመከመናወን ላይ ያሉ ሁሉን አቀፍ የልማት ስራዎች ለዚህ ጥሩ ማሳያ መሆናቸውን አንስተው የህዝቡ ጥረትና ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። ከግብርና በተጨማሪ በኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድንና የዲጂታል ልማት ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የጋራ ጥረት ይጠይቃል ብለዋል። የለውጡ መንግስት አሳታፊና ህብረ ብሔራዊ አንድነት የተረጋገጠባት ጠንካራ ሀገር የመገንባት ዓላማ ሰንቆ እየሰራ ስለመሆኑ አንስተው በዚህም እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። የፍትህ ሚኒስትሯ ሐና አርዓያስላሴ በበኩላቸው እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ማእከል ያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢዎች ገና ያልተነካ እምቅ የመልማት አቅም ያለ መሆኑን አንስተው በተለይ ወጣቶች ያለውን ፀጋ በመጠቀም በሀገራቸው ሰርተው ለመለወጥ በትጋትና በቁርጠኝነት መስራት አለባቸው ብለዋል።
በከተማው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Dec 13, 2025 109
ወላይታ ሶዶ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ህዝቡ የሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የከተማው ነዋሪዎች አመለከቱ። ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ተወካዮች በተገኙበት "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች'' በሚል መሪ ሀሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂዷል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ታደሰ ሌራ በሰጡት አስተያየት ከዚህ ቀደም ስናነሳቸው የነበሩ የልማት ጥያቄዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ምላሸ እያገኙ ነው ብለዋል። በተለይም በሰላምና ጸጥታ ዘርፍ የተሰራው ስራ የወላይታ ሶዶ ከተማን እንቅስቃሴ የተረጋጋና ሰላማዊ ማድረጉን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል በከተማው የስራ አጥነት፣ ተጀምረው ያልተጠናቀቁ የመንገድ ግንባታዎች፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት፣ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት አለመዘመን ችግሮችን ለመፍታት የተጀመሩ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል። ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ አልማዝ አንጁሉ እንደገለጹት በከተማው የህዝቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበሩ የመንገድ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሌሎችም ልማቶች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የከተማውን ውበትና እድገት የሚያፋጥን የኮሪደር ልማት ስራም እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል። ይሁንና የተጀመሩ የልማት ስራዎች ላይ መጓተት እየተስተዋለ በመሆኑ ማስተካከያ ሊደረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በከተማው የህዝብ ጥያቄን መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ ላቴኖ ላቁ ናቸው። ከተማው በርካታ ስፖርተኞች የሚወጡበት በመሆኑ ለዘመናዊ ስታዲየም ግንባታም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አመልክተዋል። የደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ችግር ለመፍታት የተጀመረው ስራ ከዳር እንዲደርስ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል። የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ በበኩላቸው የወላይታ ሶዶ ከተማ በፈጣን ዕድገት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው ከተማውን ለመለወጥ የጋራ ጥረት እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። በከተማው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የአገልግሎት አሰጣጡን ማዘመን እንደሚገባም አመልክተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከፍያለዉ ተፈራ ያለንን የሰው ኃይል፣ ለም መሬት፣ ውሃ እና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶችን በመጠቀም ለስኬታማነቱ መረባረብ ይገባል ብለዋል። የሀገርን ከፍታ የሚያረጋግጡ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲሳኩ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባም አመልክተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ተፈሪ አባተ በበኩላቸው በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም ወጣቶች የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ማግኘት የሚያስችሏቸው ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል። ህዝቡ በተደጋጋሚ ሲያነሳቸው የነበሩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው የስቴዲየም ግንባታ ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማርያም እንዳሉት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የተለያዩ የልማት ስራዎች በጥራትና በፍጥነት እየተከናወኑ ነው። ነዋሪዎችን ጭምር በማሳተፍ ከተማውን ንጹህ እና ተወዳዳሪ ለማድረግ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ከግሉ ዘርፍ ጋር በመተባበር እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተው ህዝቡ ለልማት ስራዎች ስኬታማነት የጀመረውን ተሳትፎ እንዲያጠናክር አስገንዝበዋል።
የህዝብን የልማት ተጠቃሚነትና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ረገድ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Dec 13, 2025 118
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 4/2018 (ኢዜአ) ፡-የህዝብን የልማት ተጠቃሚነትና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ረገድ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። “የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች” በሚል መሪ ሀሳብ በሀዋሳ ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። የውይይት መድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፣ በብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባት ኃላፊ ሚኒስትር አቶ መለስ ዓለሙ እና ሌሎችም የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ የተሳተፉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች በለውጡ ዓመታት ህብረብሔራዊ አንድነትን በማስጠበቅ ለህዝብ የልማት ተጠቃሚነት፣ ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ መንግስት ያደረገው ጥረት ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ዘሪሁን ቃሚሶ እና ሀጂ ኡመር ሁሴን፤ በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለህዝብ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ ብለዋል። በሲዳማ ክልል ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማት በሁሉም መስኮች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ጥረቶችም ትልቅ ተስፋ የተሰነቀባቸው መሆኑን ነው የተናገሩት። በከተሞች የኮሪደር ልማት ስራን ጨምሮ የቱሪዝም መስህብ ስፍራዎችን በማልማትና የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተከናወኑ ተግባራትም የሚደነቁ መሆናቸውን አንስተዋል። ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ ጋሻው ምትኬ (ዶ/ር)፤ በለውጡ ዓመታት በፕሮጀክቶች ክንውን፣ የግብርና ልማትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ተጨባጭ ውጤት መጥቷል ብለዋል። በመልካም አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ጥሩ ጅምሮች ቢኖሩም በቀጣይ ብዙ የተቀናጀ ሥራ ይጠይቃል ሲሉ አጽእኖት ሰጥተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ፤ የሀዋሳ ከተማን እምቅ ሃብቶች በማልማትና በማስተዋወቅ የቱሪዝምና ኢንቨስትመንት መዳረሻ የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡ የሐይቁን ዳርቻ አሁን ላይ ለነዋሪዎችና ለቱሪስቶች ምቹ ማሪፊያ በሚሆን መልኩ ደረጃ በደረጃ የማልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም አንስተዋል። የሀዋሳ ስታዲየም ግንባታን የማጠናቀቅ፣ በሀዋሳ ጉዱማሌ እየተገነባ ያለውን የባህል ማዕከል፣ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ማስፋፊያ ግንባታ፣ የታቦር ተራራ ልማትና ሌሎችም ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል። በብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ፤ መንግስት ላከናወናቸው ስራዎች ዕውቅና በመስጠት ሊሟሉ የሚገቡ ጉዳዮች መነሳታቸው በቀጣይ ለሚሰሩ የልማት ሥራዎች አስቻይ ሁኔታዎችን ይፈጥራል ብለዋል። የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች የመንግስት ትኩረቶች ሆነው ይቀጥላሉ ሲሉ ገልጸዋል። በሀዋሳ ከተማ ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አንስተው ለስኬት እንዲበቁ የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ ህዝቡም ትብብርና እገዛውን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የአማራ ክልልን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መንግስት እያደረገ ያለውን ጥረት እንደግፋለን
Dec 13, 2025 128
ባሕር ዳር ፤ ታህሳስ 4//2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልልን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መንግስት እያደረገ ያለውን ጥረት እንደግፋለን ሲሉ የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። "የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ በባህር ዳር ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሄዷል። በመድረኩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የከተማዋ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል። በመድረኩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች የክልሉን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የመንግስት ያላሰለሰ ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ የመንግስት ጥረት ውስጥ የጸጥታ አካላት፣ በየደረጃው ያለው አመራርና የህዝቡም ተሳትፎ ትልቅ መሆኑን አንስተው የከተማዋ ነዋሪዎችም ይህንኑ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ሙሉ ምትኩ፤ የለውጡ መንግስት በሁሉም አካባቢዎች ለትውልድ የሚተርፉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በማጠናቀቅ ጥቅም ላይ እያዋለ ይገኛል ብለዋል። በባህር ዳር ከተማ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በተጨባጭ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታቸው እየታየ ስለመሆኑም አንስተዋል። በመሆኑም የአማራ ክልልን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ በመሆኑ ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ወርቁ አላምረው፤ የባህር ዳርን ውበት ከጣና ሃይቅ ጋር በማስተሳሰር የጎርጎራ ግዙፍ ፕሮጀክትና ሌሎችም የልማት ስራዎችን ማድነቅ የግድ ይላል ብለዋል። እንደ ሀገር በርካታ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ክንውን እና የኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤትነት ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶችም የጋራ ተስፋ የሰነቅንባቸው ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ የዝቡጥላ ካሳ፤ በተለያዩ ችግሮች ውስጥም ሆኖ መንግስት እያከናወናቸው ያሉ የልማት ስራዎች ይበል የሚያሰኙ መሆናቸውን አንስተው በቀጣይ የኑሮ ውድነትና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ጥረት ትኩረት ይሻል ብለዋል። የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባልና የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፤ በሁሉም መስክ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር የህዝብን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች በማዳመጥ ተግባራዊ ምላሽ ከመስጠት በተጨማሪ ለችግሮች መፍትሄ የመፈለግ ስራም የመንግስት ትኩረት መሆኑን አንስተው የመድረኩም አላማ ይሄው መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የበርካታ ሀይሎች ዐይን ማረፊያ በመሆኗ ለማደግና የሕዝቦቿን ኑሮ ለመለወጥ በምታደርገው ጥረት ታሪካዊ ጠላቶች በባንዳዎች በኩል ለማሰናከል እየጣሩ መሆኑን አንስተው የተጀመረውን የለውጥና እድገት ግስጋሴ ሊያስቆማት የሚችል ሃይል የለም ብለዋል። ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ የሚነሳው ጥያቄ ተገቢ መሆኑን አንስተው መንግስት ነባራዊ ሁኔታውን ታሳቢ በማድረግ ችግሩን ለማቃለል ጥረቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በበኩላቸው፤ ባለፉት ሦስት ዓመታት ግብርናን በማዘመንና ምርታማነትን በማሳደግ ከውጭ ይገባ የነበረን ስንዴ በራስ አቅም በማምረት ማስቀረት ተችሏል ብለዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶቿ እንደተመኙት ወደ ኋላ የቀረች ሳትሆን በርካታ ተስፋ ሰጪ የልማት ስራዎችን እያከናወነች የቀጠለች መሆኑን ተናግረዋል። የአማራ ክልልን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመንግስት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው፤ የከተማዋን ሰላም የማጽናትና የልማት ስራዎችን በጥራት የማከናወኑ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። በከተማው ገበያን ለማረጋጋት አምራቹና ሸማቱ ቀጥታ የሚገናኙበት የገበያ ማዕከል እየተመቻቸ መሆኑን አንስተው፤ ምርት ያለአግባብ በሚደብቁ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑንም አመልክተዋል። በመድረኩ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ ነጋዴዎች፣ ወጣቶችና ሴቶችን ጨምሮ ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የዘላቂ ሰላም ግንባታ ጉዳይ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ ይቀጥላል
Dec 13, 2025 154
ደሴ ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የዘላቂ ሰላም ግንባታ ጉዳይ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ ሲሉ የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ቱሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በደሴ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያይተዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች ሸሕ ኢሳ ፣ወይዘሮ ብርቱካን ታደሰ እና አቶ እንድሪስ መሀመድ በሪሁን እንደገለፁት፣ መንግስት ሕብረተሰቡን በማሳተፍ ሰላምን በመጠበቅ ልማትን ለማስፋፋት የሚያደርገው ጥረት የሚደነቅ ነው። በከተማው የመንገድ አውታሮችን በማስፋት እና የስራ እድል መፍጠሪያ ሼዶች በመገንባት እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች የሚበረታቱ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ የአስፋልት መንገድ፣ መሶብ አንድ ማዕከል፣ የሕዝብ መድሃኒት ቤቶች፣ የጤና እና የትምሕርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እየተደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። በከተማው በደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ፣ በመብራት ሃይል ማነስና መቆራረጥ፣ በመሬት መንሸራተትና በክረምት ጎርፍ መከላከል ዙሪያ የሚስተዋሉ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ጠይቀዋል። ቀደም ሲል በመንግስት ቃል የተገቡና የተጀመሩ የደሴ-ኮምቦልቻ አቋራጭ መንገድ፣ ወሎ ቴሪሸሪ ኬር ሆስፒታል ግንባታ፣ አዋሽ ኮምቦልቻ ሃራ ገበያ የባቡር መንገድ ግንባታ፣ የመኖሪያ ቤት ችግር፣ ስርዓት አልበኝነት፣የኑሮ ውድነትና ስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ነው ያሉት። የሰላም ጥሪውን በማይቀበሉ ሽፍቶችና ተላላኪዎች ላይም መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉ አመልክተው፤ መንግስት በሰው ተኮር ፕሮጀክቶች የድሆችን እንባ እያበሰ በመሆኑ እኛም ሁለተናዊ ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። ሆኖም በለውጡ መንግስት ያገኘነውን ልማት ለማውደም፣ የተጀመሩን ልማቶች ለማደናቀፍ የሚታትሩ የግል ጥቅመኞችን ማስተካከል ይገባል፣ እኛም ከመንግስት ጎን ተሰልፈን ልማታችንን እናስቀጥላለን ብለዋል። ተተኪ አመራር መፍጠር፣ ወጣቱን ማብቃት፣ ለወጣቱ መዝናኛ ማመቻቸትና በከተማው ደረጃውን የጠበቀ ስታዲዮም መገንባትና የጋራ ትርክትን ማጎልበት እንደሚገባም አንስተዋል። ነዋሪዎቹ ፤ ተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የዘላቂ ሰላም ግንባታ ጉዳይ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ መቀጠል አለበት ሲሉ ተናግረዋል። ሕብረተሰቡን በማስተባበር ሰላሙን ከማስጠበቅ ባለፈ በለውጡ መንግስት ሰፋፊ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል ያሉት ደግሞ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ናቸው። በከተማው የተከናወኑ አስፋልት መንገድ፣ የኮሪደር ልማት፣ መሶብ አንድ ማዕከል፣ ሌማት ቱርፋትና ሌሎችም በለውጡ መንግስት የተከናወኑና ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ያስቸሉ የልማት ተግባራት ናቸው ብለዋል። ሕብረተሰቡ ላነሳቸው ጥያቄዎችም ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት ተገቢው ክትትልና ጥረት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍስሃ ደሳለኝ በበኩላቸው፣ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግና ሕዝቡ የድርሻውን እየተወጣ ነው ብለዋል። ግብርናውን በማዘመን፣ ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ፣ በስራ እድል ፈጠራ፣ ገበያን በማረጋጋትና በሌሎችም ሪፎርሞች ተጨባጭ ውጤት በማስመዝገብ ለሕዝብ ጥያቄ መልስ መስጠት ተችሏል ብለዋል። አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ከሰላም ጥሪው በተጓዳኝ ሕግ የማስከበር ስራው ይቀጥላል ብለዋል። የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን የበለጠ በማጠናከር የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ በመድረኩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ናቸው። በሀገሪቱ ሕግ በማስከበር ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ሂደትም ሁሉም በመደገፍ የባዳና የባንዳን ተልዕኮ ለማክሸፍ መረባረብ ይገባናል ብለዋል። የወሎን የአብሮነት፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የመረዳዳት ባሕል ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በደሴ ከተማ የተመለከትነው ልማትና ያደረግነው ውይይት ለብልጽግና ጉዟችን ተስፋ የሚሰጥ ነው ብለዋል። የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ በበኩላቸው፣ በሃገሪቱ በኢኮኖሚው፣ በማሕበራዊና በፖለቲካው ዘርፍ የተመዘገቡ ድሎች የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። በተለይ በስንዴ ልማት፣ ኮሪደር ልማት፣ ከተማ ልማት፣ በሌማት ቱርፋት፣ በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትና በሌሎችም ዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል። በውይይቱ የተነሱ ሐሳቦችንም የእቅድ አካል በማድረግ የሕብረተሰቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መልስ እንዲያገኙ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ሲሉ አረጋግጠዋል። በመድረኩም የፌዴራልና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በሕዝብና በመንግስት ጠንካራ ቅንጅት የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል የበኩላችንን እንወጣለን
Dec 13, 2025 132
ጎንደር፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ በሕዝብና በመንግስት ጠንካራ ቅንጅት የተመዘገቡ ወጤቶችን በማስቀጠል ለጉባ ብስራት የልማት ግቦች መሳካት የሚጠበቅባቸውን ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን የጎንደር ከተማ የህዝባዊ መድረክ ተሳታፊዎች ተናገሩ። በጎንደር ከተማ የተገነቡ የቅርስ ጥበቃና የመሠረት ልማት ስራዎችን በማድነቅ የንጹህ መጠጥ ውሃና የኃይል አቅርቦት፣ የዘላቂ ሰላም ግንባታና የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳዮች ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል። የተሟላ የመሠረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር የህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አረጋግጠዋል። የጎንደር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች "የጉባ ብስራቶች፥ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ ከፌዴራል፣ ክልልና ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር መክረዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረክ መልዕክታቸው፥ ኢትዮጵያ ከህዝቦቿ እሴትና ጸጋ የሚመነጭ የልማት አቅም እየፈጠረች ነው ብለዋል። የጥበብ ማማና እንግዳ አክባሪ የሆነችው ጎንደር ታሪኳን የሚመጥን የልማት ሥራ ላይ መሆኗን ገልጸዋል። በቀጣይም በኢትዮጵያ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በአራቱም ማዕዘናት በሁሉም መስክ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል የህዝብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ዘሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ለመድረኩ መነሻ በጎንደር ከተማ በአማራ ክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችና የቀጣይ የህዝብና መንግስት የልማት አቅጣጫዎችን አቅርበዋል። በዚህም ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የጎንደር ህዝብ የኢትዮጵያ አንድነትና ሕብረ ብሔራዊ ትሥሥር፣ ዘላቂ ሰላምና ሙስና፣ የመልካም አስተዳደርና ጉልህ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ሲያነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። በዚህም በጎንደር ከተማም የኢትዮጵያን የመካከለኛ ዘመን የታሪክ መነሻነት በሚመጥን መልኩ ትናንትን ከዛሬ በማስተሳሰር ዛሬን ከነገ የሚያጋምድ ልማት መሰራቱን ተናግረዋል። የክልሉና የፌዴራል መንግስት በዘላቂ ሰላም ግንባታ መርህ የጽንፈኛ ኃይሎችን የጥፋት ተልዕኮ በማክሸፍ አስተማማኝ የሕግ የበላይነት የሚያረጋግጥ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የመደመር መንግሥት ለብዝኅ ኢኮኖሚ የሰጠው ትኩረት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝምና ማዕድን መስክ በክልልና ሀገር አቀፍ ደረጃ እመርታዊ ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለ ገልጸዋል። በአጠቃላይ በክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ ፈጠራን ከፍጥነት በማሰናሰል በኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስክ የውስጥና የውጭ አሻጥርና ሴራ ያልገደበው ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት የሚያደርጉ አኩሪ ድሎች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች፥ በጎንደር ከተማ የአፄ ፋሲለደስ አብያተ መንግስት ዕድሳት፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የኮሪደርና ሌሎች የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ታሪክና ዘመናዊነትን ያሰናሰሉ ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎንደር ከተማን ታሪክ በሚመጥን መልኩ ስኬታማ የልማት ስራዎች እንዲሰሩ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የመንግስትን የሰላም አማራጭ የተቀበሉ ታጣቂዎች የክልሉንና የሀገርን ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም በንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የኃይል አቅርቦት፣ ዘላቂ ሰላም ግንባታ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የኑሮ ውድነትን የማረጋጋትና ሌሎች ምላሽ የሚሹ ጉዳዮችን ጠይቀዋል። በሀገራዊ ምክክር መፍትሔ የሚሹ የጋራ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ለጉባ ብስራት የልማት ግቦች ስኬት በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ለተነሱ ጉዳዮች በሰጡት ምላሽ፥ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በገዛ ልጆቻችን አማካኝነት የጥፋት ተልዕኳቸው ተሸካሚ እያደረጉ ነው ብለዋል። በዚህም የትህትና መገለጫ የሆነው የጎንደር ህዝብ በተሳሳተ መንገድ የቆሙ ልጆችን በመምከር የሰላም አማራጭን እንዲከተሉ የማድረግ ኃላፊነት እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። በቀጣይም የጎንደር ከተማንና የኢትዮጵያን የተሟላ የመሠረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር የህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)፥ በመድረኩ በተነሱ አስተያየትና ጥያቄዎች ለተሰሩት ዕውቅና ቀሪ ስራዎችን በማመላከት የቀረቡ ሃሳቦች የጎንደርን ህዝብ ሚዛናዊነት ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። በጎንደር የአፄ ፋሲለደስ አብያተ መንግስት ዕድሳትና የኮሪደር ልማት የተሰጠው ዕውቅና ለበለጠ የልማት ትጋት ጉልበትና ብርታት እንደሚሰጥ አስረድተዋል። በቀጣይም መንግሥት በህዝብ ተሳትፎ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ የልማት ተግባራትን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፥ የከተማዋን የልማት ትንሳኤ የሚያበስሩ ስኬቶች የጎንደር ከተማ ህዝብና መንግስት የትብብር ውጤት ናቸው ብለዋል። በቀጣይም የከተማዋ ነዋሪዎች ያነሷቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
መንግስት ሁለንተናዊ ልማትን በማረጋገጥ እድገትን ለማፋጠን የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ ቁርጠኛ ነን
Dec 13, 2025 144
ዲላ ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ):-መንግስት አሳታፊና ሁሉን አቀፍ ልማትን በማረጋገጥ የሀገርን እድገት ለማፋጠን የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ ቁርጠኛ መሆናቸውን የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በዲላ ከተማ "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተጠናቋል። ነዋሪዎቹ በውይይቱ ላይ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ በግብርናና ቱሪዝም ልማት፣ በማህበራዊ ዘርፍ፣ በአረንጓዴ አሻራ እንዲሁም በኮሪደርና በማዕድን ልማት ተጠቃሽ ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል። የሌማት ትሩፋቱ በጌዴኦ ዞንና በዲላ ከተማም በተጨባጭ እየታየ መሆኑን አንስተው መንግስት አሳታፊና ሁሉን አቀፍ ልማት በማረጋገጥ የሀገርን አድገት ለማፋጠን እያደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል። ይሁንና በሃይል አቅርቦት፣ በመንገድ መሰረተ ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በአርሶ አደር ማበረታቻና በቱሪዝም መዳረሻ ልማት ያሉ ውስንነቶች እንዲፈቱላቸው ጠይቀዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የሀገር ሽማግሌ ገብሩ ቀቀቦ፤ መንግስት እስከ ታች ወርዶ ህዝብን በማወያየት የሀገር እድገትን በጋራ ለማረጋገጥ እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል። በከተማው ህብረተሰቡን በማሳተፍ በኮሪደርና በመሰረተ ልማት ስራዎች፣ እንዲሁም በትምህርት ልማትና በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት በተከናወኑ ስራዎች መሻሻሎች እንዳሉ አንስተዋል። ይሁንና ከተማዋን ከወረዳ ጋር የሚያስተሳስሩ በፌደራልና በክልል መንግስት እንዲሁም በዞኑ አስተዳደር የተጀመሩ የመንገድ መሰረተ ልማቶች መዘግየታቸውን አንስተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የሃይል አቅርቦት ውስንነት እንዳለ የገለጹት የሀገር ሽማግሌው፣ ችግሮቹ እንዲፈቱላቸው ጠይቀዋል። መንግስት አሳታፊና ሁሉን አቀፍ ልማትን በማፋጠን ሀገርን ለማሳደግ የጀመራቸውን ስራዎች እንደሚደግፉ ያነሱት ደግሞ ሌላው ተሳታፊ ወይዘሮ ተረፈች ወራሳ ናቸው። በተለይ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት፣ ገቢና ንግድ ዘርፎችን በማዘመን የተቀላጠፈ አገልግሎት እያገኘን ነው፤ ይህም ትልቅ ለውጥና ውጤት በመሆኑ በሌሎችም ዘርፎች መጠናከር አለባቸው ብለዋል። መንግስት ህብረተሰቡን በማስተባበር የትምህርት ስብራትን ለመጠገን እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ምቹ የመማሪያ አካባቢ መፍጠሩን ያነሱት ደግሞ መምህር ፈለቀ አየለ ናቸው። የኑሮ ጫናን ለመቀነስ የደመወዝ ማሻሻያ መደረጉን በመልካምነት አንስተው፣ በከተማው በተማሪዎች ምገባ፣ በመጻህፍት አቅርቦትና በመምህራን ልማት ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተናግረዋል። ሀገራዊ የልማት ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑና ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የድርሻቸውን እንደሚወጡ ያነሱት ደግሞ አቶ ከበደ ዱሌ የተባሉ ነዋሪ ናቸው። በሥራ እድል ፈጠራ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸው ጠቅሰው በተለይ በዲላና ይርጋጨፌ ከተሞች የተገነቡ አግሮ ኢንዱስትሪዎች በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ እንዲገቡ ጠይቀዋል። የውይይት መድረኩን የመሩት የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መንግስት በልማትና በመልካም አስተዳደር ላይ የተነሱ ጥያቄዎች ተቀብሎ በየደረጃው ምላሽ ለመስጠት ይሰራል ብለዋል። ሁሉንም የልማት አቅሞች በመደመር ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን የህብረተሰቡ የላቀ ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል። በተለይም የጉባ ብስራቶችን ከግብ ለማድረስ ህብረተሰቡ በየአካባቢው ሰላሙን ከመጠበቅ ባለፈ የጀመረውን የልማት ተሳትፎ ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። የባህር በር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም አስኳል መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ ሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ በባዳዎችና ባንዳዎች እንዳይደናቀፍ ውስጣዊ አቅም ማጠናከር አለብን ብለዋል። የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በበኩላቸው፤ ጌዴኦ ከሰው ብቻ ሳይሆን ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ የሚኖር ሠላም ወዳድ ህዝብ መሆኑን አንስተዋል። ይህም ትልቅ ባህላዊ እሴት መሆኑንን ገልጸው በአካባቢው ያለውን የተፈጥር ሀብት በማልማት ለወጣቶች የሥራ እድልና ለሀገራዊ እድገት ለማዋል ይሰራል ብለዋል። የለውጡ መንግስት ወደስልጣን ከመጣ ጊዜ አንስቶ ያለምንም ልዩነት የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየመለሰ መሆኑንና ይህንንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በመድረኩ በተለያዩ የልማት ዘርፎች እንዲፈቱ ለቀረቡ ጥያቄዎች በቀጣይ ምላሽ በመስጠት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራም ገልጸዋል።
ፖለቲካ
በፀጥታና ደህንነት ተቋማት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ጉባዔዎችን በስኬት ለማስተናገድ አስችሏል
Dec 13, 2025 203
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦በፀጥታና ደህንነት ተቋማት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ዓለምአቀፍ እና አህጉራዊ ጉባዔዎች በስኬት እንዲስተናገዱ ማስቻሉን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ። የፀጥታና ደህንነት ተቋማት 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባዔ (ኮፕ- 32) በስኬት እንዲጠናቀቅ ከወዲሁ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑም ተገልጿል። "ጠንካራ የፀጥታና የደህንነት ተቋማት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ" በሚል መሪ ሃሳብ የፀጥታና የደህንነት ተቋማት የእውቅናና ምስጋና መርኃ ግብር እየተካሄደ ነው። መርኃ ግብሩ የተዘጋጀው በኢትዮጵያ የተዘጋጁ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ጉባኤዎችና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከበሩ ኃይማኖታዊና ህዝባዊ በዓላት በስኬት መጠናቀቃቸውን አስመልክቶ እንደሆነ ተገልጿል። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት በርካታ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ ጉባዔዎችን እንዲሁም ታላላቅ ሀገራዊ በዓላትን በታላቅ ስኬትና ሰላማዊ ሁኔታ ማስተናገድ ችላለች። እነዚህ ክስተቶች የሀገሪቷን የዲፕሎማሲ አቅም፣ የደህንነት ጥበቃ ብቃት እና ህዝባዊ ትብብር ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። በጸጥታና ደህንነት ተቋማት መካከል የነበረው ጠንካራ የመረጃ ልውውጥ ለስኬታማነቱ አይተኬ ሚና መጫወቱን አንስተዋል። በጉባዔዎቹ የእንግዶችን ደህንነት ከማረጋገጥ ባሻገር፣ በመዲናዋ የተረጋጋ ሁኔታን በመፍጠር ዲፕሎማሲያዊ ስራዎች ያለምንም እንቅፋት እንዲካሄዱ መደረጉን አመልክተዋል። ለዚህም በፀጥታና ደህንነት ተቋማት የተከናወኑት የሪፎርም ሥራዎች ዓለምአቀፍና አህጉራዊ ጉባዔዎችን በስኬት ለማስተናገድ አስችሏል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባዔን (ኮፕ- 32) እንድታስተናግድ መመረጧ ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን ገልፀው፤ ይህ ጉባዔ በስኬት እንዲጠናቀቅ የፀጥታና ደህንነት ተቋማት ከወዲሁ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም ለዓለም እና ለአፍሪካ ኢንተር ፖል ጉባዔም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የአፋር ክልል ህዝብ የፖለቲካ ተሳትፎና ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነቱ በተግባር እውን ሆኗል - የሰመራ ሎጊያ ነዋሪዎች
Dec 13, 2025 92
ሰመራ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የአፋር ክልል ህዝብ የፖለቲካ ተሳትፎና ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነቱ በተግባር እውን መሆኑን የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ በዛሬው ዕለት በሰመራ ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሄዷል። የመድረኩ ተሳታፊ የሰመራ ሎጊያ ነዋሪዎች ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የአፋር ክልል ህዝብ የፖለቲካ ተሳትፎና ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነቱ በተግባር እውን ሆኗል ብለዋል። በክልሉ የመስኖ ልማትን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ስራዎችም በስፋት እየተከናወኑ በመሆኑ ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የሚደረገው ጥረት እየተሳካ ስለመሆኑ አንስተዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ መሐመድ አብዱልቃድር በአፋር ክልል የተከናወኑና በመከናወን ላይ ያሉ የልማት ስራዎች ለሀገርም ጭምር የሚጠቅሙ ስለመሆናቸው ተናግረዋል። ከዚህ በፊት በነበረው የመንግስት አስተዳደር የክልሉ ህዝብ የፖለቲካ ተሳትፎና የልማት ተጠቃሚነት ፍትሃዊነት የጎደለው እንደነበር አንስተው በለውጡ እኩልነትና ፍትሃዊነት በተግባር ተረጋግጧል ብለዋል። በክልሉ ወጣቱን ማዕከል ያደረጉ የልማትና የስራ ዕድሎች እየተመቻቹ መሆኑን ያነሳው ወጣት አሊ ሰላል፤ በዚህ ረገድ ጅምሮች ቢሆኑም በቀጣይ ብዙ መሰራት እንዳለበት አንስቷል። በተለይም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርና ወንጀልን ለመከላከል ወጣቶችን በጥሩ ስነ ምግባር መቅረጽና በቂ የስራ እድል መፍጠር ይገባል ብሏል። የውይይት መድረኩን የመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)፤ በሁሉም አካባቢዎች የልማት ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል የሀገርን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ መንግስት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአፋር ክልል የተከናወኑ እና በመከመናወን ላይ ያሉ ሁሉን አቀፍ የልማት ስራዎች ለዚህ ጥሩ ማሳያ መሆናቸውን አንስተው የህዝቡ ጥረትና ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። ከግብርና በተጨማሪ በኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድንና የዲጂታል ልማት ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የጋራ ጥረት ይጠይቃል ብለዋል። የለውጡ መንግስት አሳታፊና ህብረ ብሔራዊ አንድነት የተረጋገጠባት ጠንካራ ሀገር የመገንባት ዓላማ ሰንቆ እየሰራ ስለመሆኑ አንስተው በዚህም እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። የፍትህ ሚኒስትሯ ሐና አርዓያስላሴ በበኩላቸው እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ማእከል ያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢዎች ገና ያልተነካ እምቅ የመልማት አቅም ያለ መሆኑን አንስተው በተለይ ወጣቶች ያለውን ፀጋ በመጠቀም በሀገራቸው ሰርተው ለመለወጥ በትጋትና በቁርጠኝነት መስራት አለባቸው ብለዋል።
በከተማው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Dec 13, 2025 109
ወላይታ ሶዶ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ህዝቡ የሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የከተማው ነዋሪዎች አመለከቱ። ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ተወካዮች በተገኙበት "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች'' በሚል መሪ ሀሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂዷል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ታደሰ ሌራ በሰጡት አስተያየት ከዚህ ቀደም ስናነሳቸው የነበሩ የልማት ጥያቄዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ምላሸ እያገኙ ነው ብለዋል። በተለይም በሰላምና ጸጥታ ዘርፍ የተሰራው ስራ የወላይታ ሶዶ ከተማን እንቅስቃሴ የተረጋጋና ሰላማዊ ማድረጉን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል በከተማው የስራ አጥነት፣ ተጀምረው ያልተጠናቀቁ የመንገድ ግንባታዎች፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት፣ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት አለመዘመን ችግሮችን ለመፍታት የተጀመሩ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል። ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ አልማዝ አንጁሉ እንደገለጹት በከተማው የህዝቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበሩ የመንገድ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሌሎችም ልማቶች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የከተማውን ውበትና እድገት የሚያፋጥን የኮሪደር ልማት ስራም እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል። ይሁንና የተጀመሩ የልማት ስራዎች ላይ መጓተት እየተስተዋለ በመሆኑ ማስተካከያ ሊደረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በከተማው የህዝብ ጥያቄን መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ ላቴኖ ላቁ ናቸው። ከተማው በርካታ ስፖርተኞች የሚወጡበት በመሆኑ ለዘመናዊ ስታዲየም ግንባታም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አመልክተዋል። የደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ችግር ለመፍታት የተጀመረው ስራ ከዳር እንዲደርስ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል። የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ በበኩላቸው የወላይታ ሶዶ ከተማ በፈጣን ዕድገት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው ከተማውን ለመለወጥ የጋራ ጥረት እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። በከተማው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የአገልግሎት አሰጣጡን ማዘመን እንደሚገባም አመልክተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከፍያለዉ ተፈራ ያለንን የሰው ኃይል፣ ለም መሬት፣ ውሃ እና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶችን በመጠቀም ለስኬታማነቱ መረባረብ ይገባል ብለዋል። የሀገርን ከፍታ የሚያረጋግጡ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲሳኩ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባም አመልክተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ተፈሪ አባተ በበኩላቸው በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም ወጣቶች የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ማግኘት የሚያስችሏቸው ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል። ህዝቡ በተደጋጋሚ ሲያነሳቸው የነበሩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው የስቴዲየም ግንባታ ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማርያም እንዳሉት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የተለያዩ የልማት ስራዎች በጥራትና በፍጥነት እየተከናወኑ ነው። ነዋሪዎችን ጭምር በማሳተፍ ከተማውን ንጹህ እና ተወዳዳሪ ለማድረግ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ከግሉ ዘርፍ ጋር በመተባበር እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተው ህዝቡ ለልማት ስራዎች ስኬታማነት የጀመረውን ተሳትፎ እንዲያጠናክር አስገንዝበዋል።
የህዝብን የልማት ተጠቃሚነትና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ረገድ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Dec 13, 2025 118
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 4/2018 (ኢዜአ) ፡-የህዝብን የልማት ተጠቃሚነትና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ረገድ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። “የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች” በሚል መሪ ሀሳብ በሀዋሳ ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። የውይይት መድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፣ በብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባት ኃላፊ ሚኒስትር አቶ መለስ ዓለሙ እና ሌሎችም የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ የተሳተፉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች በለውጡ ዓመታት ህብረብሔራዊ አንድነትን በማስጠበቅ ለህዝብ የልማት ተጠቃሚነት፣ ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ መንግስት ያደረገው ጥረት ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ዘሪሁን ቃሚሶ እና ሀጂ ኡመር ሁሴን፤ በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለህዝብ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ ብለዋል። በሲዳማ ክልል ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማት በሁሉም መስኮች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ጥረቶችም ትልቅ ተስፋ የተሰነቀባቸው መሆኑን ነው የተናገሩት። በከተሞች የኮሪደር ልማት ስራን ጨምሮ የቱሪዝም መስህብ ስፍራዎችን በማልማትና የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተከናወኑ ተግባራትም የሚደነቁ መሆናቸውን አንስተዋል። ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ ጋሻው ምትኬ (ዶ/ር)፤ በለውጡ ዓመታት በፕሮጀክቶች ክንውን፣ የግብርና ልማትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ተጨባጭ ውጤት መጥቷል ብለዋል። በመልካም አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ጥሩ ጅምሮች ቢኖሩም በቀጣይ ብዙ የተቀናጀ ሥራ ይጠይቃል ሲሉ አጽእኖት ሰጥተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ፤ የሀዋሳ ከተማን እምቅ ሃብቶች በማልማትና በማስተዋወቅ የቱሪዝምና ኢንቨስትመንት መዳረሻ የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡ የሐይቁን ዳርቻ አሁን ላይ ለነዋሪዎችና ለቱሪስቶች ምቹ ማሪፊያ በሚሆን መልኩ ደረጃ በደረጃ የማልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም አንስተዋል። የሀዋሳ ስታዲየም ግንባታን የማጠናቀቅ፣ በሀዋሳ ጉዱማሌ እየተገነባ ያለውን የባህል ማዕከል፣ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ማስፋፊያ ግንባታ፣ የታቦር ተራራ ልማትና ሌሎችም ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል። በብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ፤ መንግስት ላከናወናቸው ስራዎች ዕውቅና በመስጠት ሊሟሉ የሚገቡ ጉዳዮች መነሳታቸው በቀጣይ ለሚሰሩ የልማት ሥራዎች አስቻይ ሁኔታዎችን ይፈጥራል ብለዋል። የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች የመንግስት ትኩረቶች ሆነው ይቀጥላሉ ሲሉ ገልጸዋል። በሀዋሳ ከተማ ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አንስተው ለስኬት እንዲበቁ የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ ህዝቡም ትብብርና እገዛውን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የአማራ ክልልን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መንግስት እያደረገ ያለውን ጥረት እንደግፋለን
Dec 13, 2025 128
ባሕር ዳር ፤ ታህሳስ 4//2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልልን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መንግስት እያደረገ ያለውን ጥረት እንደግፋለን ሲሉ የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። "የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ በባህር ዳር ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሄዷል። በመድረኩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የከተማዋ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል። በመድረኩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች የክልሉን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የመንግስት ያላሰለሰ ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ የመንግስት ጥረት ውስጥ የጸጥታ አካላት፣ በየደረጃው ያለው አመራርና የህዝቡም ተሳትፎ ትልቅ መሆኑን አንስተው የከተማዋ ነዋሪዎችም ይህንኑ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ሙሉ ምትኩ፤ የለውጡ መንግስት በሁሉም አካባቢዎች ለትውልድ የሚተርፉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በማጠናቀቅ ጥቅም ላይ እያዋለ ይገኛል ብለዋል። በባህር ዳር ከተማ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በተጨባጭ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታቸው እየታየ ስለመሆኑም አንስተዋል። በመሆኑም የአማራ ክልልን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ በመሆኑ ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ወርቁ አላምረው፤ የባህር ዳርን ውበት ከጣና ሃይቅ ጋር በማስተሳሰር የጎርጎራ ግዙፍ ፕሮጀክትና ሌሎችም የልማት ስራዎችን ማድነቅ የግድ ይላል ብለዋል። እንደ ሀገር በርካታ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ክንውን እና የኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤትነት ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶችም የጋራ ተስፋ የሰነቅንባቸው ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ የዝቡጥላ ካሳ፤ በተለያዩ ችግሮች ውስጥም ሆኖ መንግስት እያከናወናቸው ያሉ የልማት ስራዎች ይበል የሚያሰኙ መሆናቸውን አንስተው በቀጣይ የኑሮ ውድነትና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ጥረት ትኩረት ይሻል ብለዋል። የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባልና የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፤ በሁሉም መስክ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር የህዝብን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች በማዳመጥ ተግባራዊ ምላሽ ከመስጠት በተጨማሪ ለችግሮች መፍትሄ የመፈለግ ስራም የመንግስት ትኩረት መሆኑን አንስተው የመድረኩም አላማ ይሄው መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የበርካታ ሀይሎች ዐይን ማረፊያ በመሆኗ ለማደግና የሕዝቦቿን ኑሮ ለመለወጥ በምታደርገው ጥረት ታሪካዊ ጠላቶች በባንዳዎች በኩል ለማሰናከል እየጣሩ መሆኑን አንስተው የተጀመረውን የለውጥና እድገት ግስጋሴ ሊያስቆማት የሚችል ሃይል የለም ብለዋል። ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ የሚነሳው ጥያቄ ተገቢ መሆኑን አንስተው መንግስት ነባራዊ ሁኔታውን ታሳቢ በማድረግ ችግሩን ለማቃለል ጥረቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በበኩላቸው፤ ባለፉት ሦስት ዓመታት ግብርናን በማዘመንና ምርታማነትን በማሳደግ ከውጭ ይገባ የነበረን ስንዴ በራስ አቅም በማምረት ማስቀረት ተችሏል ብለዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶቿ እንደተመኙት ወደ ኋላ የቀረች ሳትሆን በርካታ ተስፋ ሰጪ የልማት ስራዎችን እያከናወነች የቀጠለች መሆኑን ተናግረዋል። የአማራ ክልልን ሰላም ለማጽናትና የህዝቡን ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመንግስት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው፤ የከተማዋን ሰላም የማጽናትና የልማት ስራዎችን በጥራት የማከናወኑ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። በከተማው ገበያን ለማረጋጋት አምራቹና ሸማቱ ቀጥታ የሚገናኙበት የገበያ ማዕከል እየተመቻቸ መሆኑን አንስተው፤ ምርት ያለአግባብ በሚደብቁ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑንም አመልክተዋል። በመድረኩ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ ነጋዴዎች፣ ወጣቶችና ሴቶችን ጨምሮ ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የዘላቂ ሰላም ግንባታ ጉዳይ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ ይቀጥላል
Dec 13, 2025 154
ደሴ ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የዘላቂ ሰላም ግንባታ ጉዳይ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ ሲሉ የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ቱሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በደሴ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያይተዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች ሸሕ ኢሳ ፣ወይዘሮ ብርቱካን ታደሰ እና አቶ እንድሪስ መሀመድ በሪሁን እንደገለፁት፣ መንግስት ሕብረተሰቡን በማሳተፍ ሰላምን በመጠበቅ ልማትን ለማስፋፋት የሚያደርገው ጥረት የሚደነቅ ነው። በከተማው የመንገድ አውታሮችን በማስፋት እና የስራ እድል መፍጠሪያ ሼዶች በመገንባት እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች የሚበረታቱ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ የአስፋልት መንገድ፣ መሶብ አንድ ማዕከል፣ የሕዝብ መድሃኒት ቤቶች፣ የጤና እና የትምሕርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እየተደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። በከተማው በደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ፣ በመብራት ሃይል ማነስና መቆራረጥ፣ በመሬት መንሸራተትና በክረምት ጎርፍ መከላከል ዙሪያ የሚስተዋሉ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ጠይቀዋል። ቀደም ሲል በመንግስት ቃል የተገቡና የተጀመሩ የደሴ-ኮምቦልቻ አቋራጭ መንገድ፣ ወሎ ቴሪሸሪ ኬር ሆስፒታል ግንባታ፣ አዋሽ ኮምቦልቻ ሃራ ገበያ የባቡር መንገድ ግንባታ፣ የመኖሪያ ቤት ችግር፣ ስርዓት አልበኝነት፣የኑሮ ውድነትና ስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ነው ያሉት። የሰላም ጥሪውን በማይቀበሉ ሽፍቶችና ተላላኪዎች ላይም መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉ አመልክተው፤ መንግስት በሰው ተኮር ፕሮጀክቶች የድሆችን እንባ እያበሰ በመሆኑ እኛም ሁለተናዊ ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። ሆኖም በለውጡ መንግስት ያገኘነውን ልማት ለማውደም፣ የተጀመሩን ልማቶች ለማደናቀፍ የሚታትሩ የግል ጥቅመኞችን ማስተካከል ይገባል፣ እኛም ከመንግስት ጎን ተሰልፈን ልማታችንን እናስቀጥላለን ብለዋል። ተተኪ አመራር መፍጠር፣ ወጣቱን ማብቃት፣ ለወጣቱ መዝናኛ ማመቻቸትና በከተማው ደረጃውን የጠበቀ ስታዲዮም መገንባትና የጋራ ትርክትን ማጎልበት እንደሚገባም አንስተዋል። ነዋሪዎቹ ፤ ተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ የዘላቂ ሰላም ግንባታ ጉዳይ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ መቀጠል አለበት ሲሉ ተናግረዋል። ሕብረተሰቡን በማስተባበር ሰላሙን ከማስጠበቅ ባለፈ በለውጡ መንግስት ሰፋፊ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል ያሉት ደግሞ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ናቸው። በከተማው የተከናወኑ አስፋልት መንገድ፣ የኮሪደር ልማት፣ መሶብ አንድ ማዕከል፣ ሌማት ቱርፋትና ሌሎችም በለውጡ መንግስት የተከናወኑና ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ያስቸሉ የልማት ተግባራት ናቸው ብለዋል። ሕብረተሰቡ ላነሳቸው ጥያቄዎችም ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት ተገቢው ክትትልና ጥረት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍስሃ ደሳለኝ በበኩላቸው፣ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግና ሕዝቡ የድርሻውን እየተወጣ ነው ብለዋል። ግብርናውን በማዘመን፣ ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ፣ በስራ እድል ፈጠራ፣ ገበያን በማረጋጋትና በሌሎችም ሪፎርሞች ተጨባጭ ውጤት በማስመዝገብ ለሕዝብ ጥያቄ መልስ መስጠት ተችሏል ብለዋል። አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ከሰላም ጥሪው በተጓዳኝ ሕግ የማስከበር ስራው ይቀጥላል ብለዋል። የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን የበለጠ በማጠናከር የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ በመድረኩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ናቸው። በሀገሪቱ ሕግ በማስከበር ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ሂደትም ሁሉም በመደገፍ የባዳና የባንዳን ተልዕኮ ለማክሸፍ መረባረብ ይገባናል ብለዋል። የወሎን የአብሮነት፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የመረዳዳት ባሕል ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በደሴ ከተማ የተመለከትነው ልማትና ያደረግነው ውይይት ለብልጽግና ጉዟችን ተስፋ የሚሰጥ ነው ብለዋል። የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ በበኩላቸው፣ በሃገሪቱ በኢኮኖሚው፣ በማሕበራዊና በፖለቲካው ዘርፍ የተመዘገቡ ድሎች የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። በተለይ በስንዴ ልማት፣ ኮሪደር ልማት፣ ከተማ ልማት፣ በሌማት ቱርፋት፣ በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትና በሌሎችም ዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል። በውይይቱ የተነሱ ሐሳቦችንም የእቅድ አካል በማድረግ የሕብረተሰቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መልስ እንዲያገኙ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ሲሉ አረጋግጠዋል። በመድረኩም የፌዴራልና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በሕዝብና በመንግስት ጠንካራ ቅንጅት የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል የበኩላችንን እንወጣለን
Dec 13, 2025 132
ጎንደር፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ በሕዝብና በመንግስት ጠንካራ ቅንጅት የተመዘገቡ ወጤቶችን በማስቀጠል ለጉባ ብስራት የልማት ግቦች መሳካት የሚጠበቅባቸውን ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን የጎንደር ከተማ የህዝባዊ መድረክ ተሳታፊዎች ተናገሩ። በጎንደር ከተማ የተገነቡ የቅርስ ጥበቃና የመሠረት ልማት ስራዎችን በማድነቅ የንጹህ መጠጥ ውሃና የኃይል አቅርቦት፣ የዘላቂ ሰላም ግንባታና የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳዮች ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል። የተሟላ የመሠረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር የህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አረጋግጠዋል። የጎንደር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች "የጉባ ብስራቶች፥ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ ከፌዴራል፣ ክልልና ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር መክረዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረክ መልዕክታቸው፥ ኢትዮጵያ ከህዝቦቿ እሴትና ጸጋ የሚመነጭ የልማት አቅም እየፈጠረች ነው ብለዋል። የጥበብ ማማና እንግዳ አክባሪ የሆነችው ጎንደር ታሪኳን የሚመጥን የልማት ሥራ ላይ መሆኗን ገልጸዋል። በቀጣይም በኢትዮጵያ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በአራቱም ማዕዘናት በሁሉም መስክ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል የህዝብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ዘሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ለመድረኩ መነሻ በጎንደር ከተማ በአማራ ክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችና የቀጣይ የህዝብና መንግስት የልማት አቅጣጫዎችን አቅርበዋል። በዚህም ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የጎንደር ህዝብ የኢትዮጵያ አንድነትና ሕብረ ብሔራዊ ትሥሥር፣ ዘላቂ ሰላምና ሙስና፣ የመልካም አስተዳደርና ጉልህ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ሲያነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። በዚህም በጎንደር ከተማም የኢትዮጵያን የመካከለኛ ዘመን የታሪክ መነሻነት በሚመጥን መልኩ ትናንትን ከዛሬ በማስተሳሰር ዛሬን ከነገ የሚያጋምድ ልማት መሰራቱን ተናግረዋል። የክልሉና የፌዴራል መንግስት በዘላቂ ሰላም ግንባታ መርህ የጽንፈኛ ኃይሎችን የጥፋት ተልዕኮ በማክሸፍ አስተማማኝ የሕግ የበላይነት የሚያረጋግጥ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የመደመር መንግሥት ለብዝኅ ኢኮኖሚ የሰጠው ትኩረት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝምና ማዕድን መስክ በክልልና ሀገር አቀፍ ደረጃ እመርታዊ ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለ ገልጸዋል። በአጠቃላይ በክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ ፈጠራን ከፍጥነት በማሰናሰል በኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስክ የውስጥና የውጭ አሻጥርና ሴራ ያልገደበው ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት የሚያደርጉ አኩሪ ድሎች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች፥ በጎንደር ከተማ የአፄ ፋሲለደስ አብያተ መንግስት ዕድሳት፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የኮሪደርና ሌሎች የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ታሪክና ዘመናዊነትን ያሰናሰሉ ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎንደር ከተማን ታሪክ በሚመጥን መልኩ ስኬታማ የልማት ስራዎች እንዲሰሩ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የመንግስትን የሰላም አማራጭ የተቀበሉ ታጣቂዎች የክልሉንና የሀገርን ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም በንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የኃይል አቅርቦት፣ ዘላቂ ሰላም ግንባታ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የኑሮ ውድነትን የማረጋጋትና ሌሎች ምላሽ የሚሹ ጉዳዮችን ጠይቀዋል። በሀገራዊ ምክክር መፍትሔ የሚሹ የጋራ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ለጉባ ብስራት የልማት ግቦች ስኬት በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ለተነሱ ጉዳዮች በሰጡት ምላሽ፥ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በገዛ ልጆቻችን አማካኝነት የጥፋት ተልዕኳቸው ተሸካሚ እያደረጉ ነው ብለዋል። በዚህም የትህትና መገለጫ የሆነው የጎንደር ህዝብ በተሳሳተ መንገድ የቆሙ ልጆችን በመምከር የሰላም አማራጭን እንዲከተሉ የማድረግ ኃላፊነት እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። በቀጣይም የጎንደር ከተማንና የኢትዮጵያን የተሟላ የመሠረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር የህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)፥ በመድረኩ በተነሱ አስተያየትና ጥያቄዎች ለተሰሩት ዕውቅና ቀሪ ስራዎችን በማመላከት የቀረቡ ሃሳቦች የጎንደርን ህዝብ ሚዛናዊነት ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። በጎንደር የአፄ ፋሲለደስ አብያተ መንግስት ዕድሳትና የኮሪደር ልማት የተሰጠው ዕውቅና ለበለጠ የልማት ትጋት ጉልበትና ብርታት እንደሚሰጥ አስረድተዋል። በቀጣይም መንግሥት በህዝብ ተሳትፎ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ የልማት ተግባራትን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፥ የከተማዋን የልማት ትንሳኤ የሚያበስሩ ስኬቶች የጎንደር ከተማ ህዝብና መንግስት የትብብር ውጤት ናቸው ብለዋል። በቀጣይም የከተማዋ ነዋሪዎች ያነሷቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
መንግስት ሁለንተናዊ ልማትን በማረጋገጥ እድገትን ለማፋጠን የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ ቁርጠኛ ነን
Dec 13, 2025 144
ዲላ ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ):-መንግስት አሳታፊና ሁሉን አቀፍ ልማትን በማረጋገጥ የሀገርን እድገት ለማፋጠን የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ ቁርጠኛ መሆናቸውን የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በዲላ ከተማ "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተጠናቋል። ነዋሪዎቹ በውይይቱ ላይ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ በግብርናና ቱሪዝም ልማት፣ በማህበራዊ ዘርፍ፣ በአረንጓዴ አሻራ እንዲሁም በኮሪደርና በማዕድን ልማት ተጠቃሽ ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል። የሌማት ትሩፋቱ በጌዴኦ ዞንና በዲላ ከተማም በተጨባጭ እየታየ መሆኑን አንስተው መንግስት አሳታፊና ሁሉን አቀፍ ልማት በማረጋገጥ የሀገርን አድገት ለማፋጠን እያደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል። ይሁንና በሃይል አቅርቦት፣ በመንገድ መሰረተ ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በአርሶ አደር ማበረታቻና በቱሪዝም መዳረሻ ልማት ያሉ ውስንነቶች እንዲፈቱላቸው ጠይቀዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የሀገር ሽማግሌ ገብሩ ቀቀቦ፤ መንግስት እስከ ታች ወርዶ ህዝብን በማወያየት የሀገር እድገትን በጋራ ለማረጋገጥ እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል። በከተማው ህብረተሰቡን በማሳተፍ በኮሪደርና በመሰረተ ልማት ስራዎች፣ እንዲሁም በትምህርት ልማትና በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት በተከናወኑ ስራዎች መሻሻሎች እንዳሉ አንስተዋል። ይሁንና ከተማዋን ከወረዳ ጋር የሚያስተሳስሩ በፌደራልና በክልል መንግስት እንዲሁም በዞኑ አስተዳደር የተጀመሩ የመንገድ መሰረተ ልማቶች መዘግየታቸውን አንስተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የሃይል አቅርቦት ውስንነት እንዳለ የገለጹት የሀገር ሽማግሌው፣ ችግሮቹ እንዲፈቱላቸው ጠይቀዋል። መንግስት አሳታፊና ሁሉን አቀፍ ልማትን በማፋጠን ሀገርን ለማሳደግ የጀመራቸውን ስራዎች እንደሚደግፉ ያነሱት ደግሞ ሌላው ተሳታፊ ወይዘሮ ተረፈች ወራሳ ናቸው። በተለይ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት፣ ገቢና ንግድ ዘርፎችን በማዘመን የተቀላጠፈ አገልግሎት እያገኘን ነው፤ ይህም ትልቅ ለውጥና ውጤት በመሆኑ በሌሎችም ዘርፎች መጠናከር አለባቸው ብለዋል። መንግስት ህብረተሰቡን በማስተባበር የትምህርት ስብራትን ለመጠገን እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ምቹ የመማሪያ አካባቢ መፍጠሩን ያነሱት ደግሞ መምህር ፈለቀ አየለ ናቸው። የኑሮ ጫናን ለመቀነስ የደመወዝ ማሻሻያ መደረጉን በመልካምነት አንስተው፣ በከተማው በተማሪዎች ምገባ፣ በመጻህፍት አቅርቦትና በመምህራን ልማት ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተናግረዋል። ሀገራዊ የልማት ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑና ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የድርሻቸውን እንደሚወጡ ያነሱት ደግሞ አቶ ከበደ ዱሌ የተባሉ ነዋሪ ናቸው። በሥራ እድል ፈጠራ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸው ጠቅሰው በተለይ በዲላና ይርጋጨፌ ከተሞች የተገነቡ አግሮ ኢንዱስትሪዎች በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ እንዲገቡ ጠይቀዋል። የውይይት መድረኩን የመሩት የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መንግስት በልማትና በመልካም አስተዳደር ላይ የተነሱ ጥያቄዎች ተቀብሎ በየደረጃው ምላሽ ለመስጠት ይሰራል ብለዋል። ሁሉንም የልማት አቅሞች በመደመር ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን የህብረተሰቡ የላቀ ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል። በተለይም የጉባ ብስራቶችን ከግብ ለማድረስ ህብረተሰቡ በየአካባቢው ሰላሙን ከመጠበቅ ባለፈ የጀመረውን የልማት ተሳትፎ ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። የባህር በር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም አስኳል መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ ሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ በባዳዎችና ባንዳዎች እንዳይደናቀፍ ውስጣዊ አቅም ማጠናከር አለብን ብለዋል። የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በበኩላቸው፤ ጌዴኦ ከሰው ብቻ ሳይሆን ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ የሚኖር ሠላም ወዳድ ህዝብ መሆኑን አንስተዋል። ይህም ትልቅ ባህላዊ እሴት መሆኑንን ገልጸው በአካባቢው ያለውን የተፈጥር ሀብት በማልማት ለወጣቶች የሥራ እድልና ለሀገራዊ እድገት ለማዋል ይሰራል ብለዋል። የለውጡ መንግስት ወደስልጣን ከመጣ ጊዜ አንስቶ ያለምንም ልዩነት የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየመለሰ መሆኑንና ይህንንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በመድረኩ በተለያዩ የልማት ዘርፎች እንዲፈቱ ለቀረቡ ጥያቄዎች በቀጣይ ምላሽ በመስጠት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራም ገልጸዋል።
ማህበራዊ
የወጣቶች አደረጃጀቶች በበጎ ፍቃድ ደም ከመለገስ ባሻገር የማህበረሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ላይ ተሳትፎአቸውን እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ
Dec 14, 2025 23
አዳማ፤ ታህሳስ 5/2018(ኢዜአ)፡-የወጣት አደረጃጀቶች በበጎ ፍቃድ ደም ከመለገስ ባሻገር የማህበረሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ላይ ተሳትፎአቸውን እንዲያጠናክሩ የኢትዮጵያ ደምና ሕብረህዋስ አገልግሎት ጠየቀ። አገልግሎቱ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ደም ለጋሽ ማህበር ጋር ባለፉት አምስት ወራት ያከናወናቸውን የደም አሰባሰብ ሂደትና የቀጣይ በጋ ወራት የደም አሰባሰብ ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዳማ አካሄደዋል ። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አሸናፊ ታዘበው እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ 550 ሺህ ዩኒቲ ደም ለመሰብሰብ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን ጨምሮ ተማሪዎች፣ የኃይማኖት ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው። ለተግባራዊነቱም የማህበረሰቡን የደም የመለገስ ባህል ለማሳደግ የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶችና ትምህርት ቤቶች በማሳተፍ ባለፉት አምስት ወራት 202 ሺህ ዩኒቲ ደም ተሰብስቧል ብለዋል። የበጎ ፈቃድ ስራውን በበጋ ወራት ለማስቀጠል የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶች ከሚያደርጉት የበጎ ፍቃድ የደም ልገሳ ባሻገር ህብረተሰቡን በማስገንዘብ ረገድ ያላቸውን ሚና እንዲያጠናክሩ መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። አገልግሎቱ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ጂማ እና ጂግጅጋን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች ቋሚ ደምለጋሽ አባላት ማፍራቱን አንስተዋል። ወጣቶቹ በበጎ ፈቃድ በሚለግሱት ደም ሌሎች እንዲሳተፉ የንቅናቄ ተግባር ላይ በመሳተፍ ህይወት እያዳኑ ነው ብለዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ሙሉጌታ እንዳለ በበኩላቸው የመዲናዋን የጤና ተቋማት የደም ፍላጎት ለማሟላት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በደም እጦት ምክንያት የሚሞቱ እናቶችና ዜጎችን ቁጥር ዜሮ ማድረግ እንደተቻለ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ደም ለጋሽ ማህበር አስተባባሪ ወጣት ነቢዩ ሙሰማ በበኩሉ ማህበሩ በደም እጦት የሚሞቱ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ አባላቱን በማስተባበር ደም እያሰባሰበ ይገኛል ብለዋል። ማህበሩ በየሶስት ወሩ በቋሚነት ከሚሰበሰበው ደም በተጨማሪ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ደም እንዲለግሱ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ባለፉት አምስት ወራት ማህበሩ ሲያከናውን የቆየውን የደም ልገሳ በበጋ ወራት ለማጠናከር ማቀዱን ጠቁመዋል።
ረቂቅ ደንቡ በእውቀትና በመልካም ስብዕና የታነጸ ትውልድን ለመገንባት አቅም የሚፈጥር ነው
Dec 14, 2025 64
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 5/2018(ኢዜአ)፦በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከል የተዘጋጀው ረቂቅ ደንብና የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ በእውቀትና በመልካም ስብዕና የታነጸ ትውልድን ለመገንባት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩ በአዲስ አበባ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ገለጹ። ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ቤቶች አካባቢ የሚስተዋሉ አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል ረቂቅ ደንብ በማዘጋጀት ተግባር ላይ ለማዋል እንቅስቃሴ ጀምሯል። በተመሳሳይ ተማሪዎችን በመልካም ስብዕና ለማነጽ እንደሚያስችል የታመነበት የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጅቷል። በደንብና መመሪያዎቹ የተለያዩ የሱስ አይነቶች መጠቀምና መሸጥ፣ የኢትዮጵያን ባህል፣ ወግና እሴትን የማይገልፁ የውጭ የሆኑ በዓላትን ማክበር፣ ስልክ ይዞ ወደ ትምህርት ቤት መግባት፣ የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያውክ የድምፅ ብክለትን፣የቁማር መጫወቻ ቦታዎችን በትምህርት ቤት አቅራቢያ መክፈት እንደማይፈቀድ ተቀምጧል። የድል በር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደጀኔ ተስፋዬ በመማር ማስተማር ሂደት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እያሳደሩ ካሉ ፈተናዎች መካከል በትምህርት ተቋማት አካባቢ የሚገኙ አዋኪ ድርጊቶች ቀዳሚዎች መሆናቸውን ይናገራሉ። እነዚህ ቦታዎች በአንዳንድ ተማሪዎች ላይ ለሚስተዋሉ የስነ ምግባር ግድፈቶች ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውን ጠቅሰዋል። መንግሥት የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት በትምህርት ቤቶች አካባቢ የሚስተዋሉ አዋኪ ድርጊቶችን ለመቆጣጠር ረቂቅ ደንብ እና የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ ማውጣቱ ተገቢ ነው ይላሉ። ረቂቅ ደንቡና መመሪያው ተማሪዎች ከትምህርታቸው ወደ ኋላ ከሚያስቀሯቸው አዋኪ ነገሮች በመራቅ በትምህርታቸው እንዲተጉ ጉልህ ሚና እንደሚያበረክቱም ጠቁመዋል። የአሚጎኒያን ትምህርት ቤት አካዳሚክ ዳይሬክተር ኤሳው አለማየሁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የትምህርት ተቋማትን ቀጣይነት ባለው ሁኔታ ከልዩ ልዩ አዋኪ ድርጊቶች ማላቀቅ ካልተቻለ ሀገርን የሚገነባ ብቁ ዜጋ ማፍራት አዳጋች መሆኑን አንስተዋል። ከአዋኪ ድርጊቶችና ከስነ ምግባር ጋር በተገናኘ በትምህርት ቤቶች የሚታዩ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ረቂቅ ደንብና መመሪያ መውጣቱ የሚበረታታ ጉዳይ ነው ብለዋል። ረቂቅ ደንቡና መመሪያው በተገቢው መልኩ ዳብረው ወደ ተግባር እንዲገቡ የዘርፉ ተዋናዮች የሚጠበቅብንን ሀገራዊ ኃላፊነት መወጣት አለብን ነው ያሉት። አስተያየት ሰጪዎቹ አይይዘውም ረቂቅ ደንቡና መመሪያው ኢትዮጵያ ያላትን ባህል፣ ወግ እና እሴት በተገቢው መንገድ ለመጠበቅ ፋይዳ እንዳለውም አመላክተዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ፥ መንግስት ተማሪዎች ምቹ በሆኑ የመማር ማስተማር አካባቢዎች እውቀት የሚገበዩበትን ሁኔታ ለመፍጠር የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጸዋል። እየተከናወኑ ካሉ አበይት ክንውኖች መካከል የትምህርት ስርዓቱን የሚጎዱ አዋኪ ድርጊቶችን መከላከል የሚያስችል አሰራር እየተዘረጋ ነው ብለዋል። በትምህርት ቤቶች አካባቢ የሚስተዋሉ አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል ረቂቅ ደንብ መዘጋጀቱን በማውሳት። ይህም የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና ተማሪዎች መልካም ስነ ምግባር የተላበሱ እንዲሆኑ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ነው ያሉት።
በክልሉ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የወባ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ሥራ ውጤት እያመጣ ነው
Dec 13, 2025 111
ወልቂጤ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰቡን ያሳተፈ የወባ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ሥራ ውጤት እያመጣ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡ "ወባን ማጥፋት ከእኔ ይጀምራል" በሚል መሪ ሀሳብ በጉራጌ ዞን ቸሃ ወረዳ በአዶሼና አቶርቸ ቀበሌ የወባ ሳምንት ተከብሯል። የክልሉ ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወነው የወባ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ሥራ ውጤት እያመጣ ነው፡፡ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስ የጤና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን በማጠናከር የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሳደግ፣ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማፋሰስና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የአልጋ አጎበር ስርጭትና የጸረ ወባ ኬሚካል ርጭት መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ በጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ህይወት ሰለሞን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት የወባ በሽታን ለመከላከልና ስርጭቱን ለመቀነስ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም ስራውን አጠናክሮ በማስቀጠል የወባ በሽታን ለማጥፋት ባለድርሻ አካላትን ላሳተፈ ቅንጀታዊ ሥራ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል፡፡ እንደ ህይወት (ዶ/ር) ገለጻ፤ ባለፈው ዓመት በ222 ወረዳዎች የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከል የጸረ ወባ ኬሚካል ርጭት የተካሄደ ሲሆን 5 ነጥብ 9 ሚሊዮን አጎበርም ለህብረተሰቡ ተሰራጭቷል። በዚህ ዓመትም ህብረተሰቡን በማሳተፍ ውሃ ያቆሩ ስፍራዎችን የማዳፈን፣ የአልጋ አጎበሮችን የማሰራጨትና የጸረ ወባ ኬሚካል ርጭት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አክለዋል። በዞኑ 11 ወረዳዎች የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ትኩረት ተድርጎ እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ አየለ ፈቀደ ናቸው። የበሽታውን ስርጭት ለመከላከልና ለመቆጣጠር ህብረተሰቡን ያሳተፈ የመከላከልና የግንዛቤ ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡ በቸሃ ወረዳ የአዶሼና አቶርቸ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ እድሉ ገብሬ፤ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በሚሰጧቸው ሙያዊ ምክር ታግዘው የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን የማጽዳትና ውሀ የሚያቁሩ ስፍራዎችን የማዳፈን ሥራ ማከናወናቸውን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡ በወባ መራቢያ መንገዶች ላይ ግንዛቤ ማግኘቱ አካባቢውን በጋራ ከማጽዳት ባለፈ የአልጋ አጎበርን በመጠቀም ራሱን ከወባ በሽታ ለመጠበቅ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ የጤና ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የተከበረው የወባ ሳምንት እንደ ሃገር ለ7ኛ ጊዜ እንደ ክልል ደግሞ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑ ታውቋል።
አቅመ ደካማ ወገኖችንና የሀገር ባለውለታዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሰው ተኮር ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Dec 13, 2025 134
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ አቅመ ደካማ ወገኖችንና የሀገር ባለውለታዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሰው ተኮር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በልደታ ክፍለ ከተማ 106 የቀበሌ ቤቶችን ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው አቅመ ደካሞች፣ ለአካል ጉዳተኞችና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚኖሩ የሀገር ባለውለታዎች በእጣ አስረክበዋል። በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክትም ከተማ አስተዳደሩ ለዘመናት የቆዩ ተደራራቢ ችግሮችን ለማቃለልና በድሕነት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር ለሆኑ የልማት ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የዚህም ዋነኛ ዓላማ የዜጎችን አጠቃላይ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻልና ከተማዋን ማዘመን እንደሆነም ነው ያመለከቱት። በመዲናዋ በተከናወኑ የሰው ተኮር የልማት ስራዎች እስካሁን ከ40 ሺህ በላይ የከተማዋ አቅመ ደካማ ወገኖችን የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በመዲናዋ የሚከናወኑ ማህበራዊ የልማት ፕሮግራሞች ለነዋሪዎች ሰው ተኮር አገልግሎት በማቅረብ ረገድ ከተማ አስተዳደሩ በቁርጠኝነት እየሠራ መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። በመዲናዋ የዜጎችን ሕይወት የሚያሻሽሉ የመኖሪያ ቤት ልማትና ሌሎች በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። መኖሪያ ቤት የተሰጣቸው ወገኖች በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ በሰው ተኮር ሥራዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረጉ አመስግነዋል።
ኢኮኖሚ
በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በመሰማራት ተኪ ምርት ላይ በማተኮራችን ውጤታማ ሆነናል-ማህበራት
Dec 14, 2025 39
ወልቂጤ፤ታህሳስ 5/2018 (ኢዜአ):-በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በመሰማራት ተኪ ምርት ላይ በማተኮራቸው ውጤታማ መሆናቸውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዘርፉ የተሰማሩ ማህበራት ተናገሩ። የክልሉ ስራ እድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ በበኩሉ በተለያዩ የስራ ዘርፎች የሚሰማሩ ዜጎች ውጤታማ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፆ፥በተያዘው ዓመት ለ400 ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጠር ይሆናል ብሏል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተደራጁ ማህበራት በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ተኪ ምርቶችን በማምረት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በሆሳዕና ከተማ የሚገኘው የዋቻሞ ኢንተርፕራይዝ ተወካይ ወይዘሪት ምስጋና ዝግዴ ከዓመት በፊት ለ5 ተደራጅተው ቡና በዘመናዊ ማሽን በመፍጨትና ቆልቶ በማሸግ ስራ ላይ መሰማራታቸውን ተናግራለች። መንግስት ወደዚህ ስራ እንዲገቡ ክህሎታቸውን ከማሳደግ ባለፈ የመስሪያ ቦታ እንዳመቻቸላቸው ገልፃ፥ የቡና ምርቱን ከሃገር አልፎ ወደ ውጭ በመላክ የገበያ ትስስራቸው መስፋቱን አንስታለች። በመቶ ሺህ ብር የጀመሩት ካፒታል አሁን ላይ ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ መድረሱን ገልጻ፥በዚህም ኢኮኖሚያቸውን በማሳደግ ለ30 ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግራለች። በቡታጅራ ከተማ የሚገኘው የአግኖት የሳሙናና እና ዲተርጀንት ማምረቻ ማህበር ሰብሳቢ ወይዘሮ አይዳ ወልጫፎ በበኩላቸው፥ ሶስት ሆነው የጀመሩት ስራ ውጤታማ ሆኖ ምርታቸውን ለገበያ ማቅረብ መጀመራቸውን ገልጸዋል። ምርቱን ለማምረት ሁሉም ግብአቶች በሃገር ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን ገልጸው፥በዚህም ከውጭ ይገቡ የነበሩ ሳሙናና የንፅህና መጠበቂያ ዲተርጀንቶችን በሃገር ውስጥ ማምረት መቻላቸውን ተናግረዋል። የተፈጠረው የገበያ ትስስር ውጤታማ እንዳደረጋቸው እና በስፋት ለመስራት እያነሳሳቸው መሆኑን አመልክተዋል። መንግስት የመነሻ ብድርና የመስሪያ ቦታ እንዲሁም የሊዝ ማሽን በማቅረቡ ወደ ስራ መግባታቸውን የገለፁት ደግሞ በክልሉ በመስቃን ወረዳ በቤትና በቢሮ ዕቃዎች ምርት ላይ የተሰማሩት አቶ ማረኝ ደመቀ ናቸው። በዚህም ከውጭ ይገቡ የነበሩ የቤትና የቢሮ መገልገያ የእንጨት ውጤቶችን በማምረት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ፥ በክልሉ ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት በማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ውጤት እየተገኘ ነው ብለዋል፡፡ ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ በማድረግ የተገኘውን ውጤት የማስቀጠል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፥ ዘርፉ ለበርካቶች የስራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ለ400 ሺህ ስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጠር የገለጹት አቶ ሙስጠፋ፥ ባለፉት ወራት ውስጥ ከ193 ሺህ 104 ዜጎች በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፈጠሩን ገልፀዋል። የክህሎት ስልጠና፣የገበያ ትስስር መፍጠር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታዎችን ማመቻቸት እንዲሁም ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበት ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
ለቡና ልማት፣ ጥራትና ግብይት የተሰጠው ትኩረት አምራቹን ተጠቃሚ በማድረግ ለሀገርም የውጭ ምንዛሪ ገቢ እያሳደገ ነው
Dec 14, 2025 48
አዶላ፤ ታህሳስ 5.2018(ኢዜአ) ፡- ለቡና ልማት፣ ጥራትና ግብይት የሰጠው ትኩረት አምራቹን ተጠቃሚ በማድረግ ለሀገርም የውጪ ምንዛሪ ገቢ እያሳደገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ገለጸ። በጉጂ ዞን አዶላ ወዩ ዙሪያ ወረዳ ቢርቢርሳ ቢሉ ቀበሌ የተቋቋመው የቡና ጣዕም ቅምሻ ማዕከል የፌዴራል እና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር)፣ ባለፉት ዓመታት መንግስት ለቡና ልማት፣ ጥራትና ግብይት የሰጠው ትኩረት አምራቹን ተጠቃሚ እያደረገ ለሀገርም የውጭ ምንዛሪ ገቢ እያሳደገ መምጣቱን ተናግረዋል። በተለይም በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሻሻሉ የቡና ችግኝ ዝርያን በመጠቀም የቡና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች በተከታታይ ሲሰሩ ቆይተዋል ብለዋል። የቡና ምርትን በጥራት ለማሳደግ አምራች አርሶ አደሮችን፣ ነጋዴዎችንና ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የግንዛቤ ማሳደግ ስራዎች በሁሉም አካባቢዎች መሰራቱን አውስተዋል። በዚህም መሰረት ባለፈው ዓመት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የቀረበ የቡና ምርት ማሳደግ መቻሉን ገልጸው፤ ዘንድሮም የተሻለ ምርት እንደሚሰበሰብ ይጠበቃል ብለዋል። የኦሮሚያ ክልልም የቡና ምርት በስፋት ከሚሰበስብባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ትልቁ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም የጉጂ ቡና በተፈጥሮ ጣዕምና ጥራቱ ከሀገር አልፎ በአለም ገበያ ይበልጥ አዋጭ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። በዞኑ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የቡና ጣዕም መቅመሻ ማዕከልም በአካባቢው የሚመመረተው ቡና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለገበያ እንዲቀርብ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው አመልክተዋል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ፣ በክልሉ የቡና ምርታማነትን የማሳደግ እና ጥራትን የማስጠበቅ ስራዎች ውጤታማ እየሆኑ መጥተዋል ብለዋል። ከክልሉ ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ ምርት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የቡና ጣዕም ቅምሻ ማዕከሉ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል። የጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ነጋሽ ቡላላ በበኩላቸው ከዞኑ ባለፈው ዓመት ከ70 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን አስታውሰዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም ከዞኑ ከ120 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን ጠቅሰው፤ በዞኑ ከ160 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች የቡና ልማት ተሳታፊና ተጠቃሚእንደሆኑና ከ473 ሺህ ሄክታር በላይ በቡና ሊለማ የሚችል ሰፊ መሬት መኖሩን አመላክተዋል፡፡ በዞኑ የተቋቋመው የቡና ጥራትና ጣዕም ቅምሻ ማዕከል አምራቹን ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ በዞኑ አዶላ ሬዴ ወረዳ የአንፈራራ ቀበሌ ቡና አምራች አቶ ታሪኩ መራሚ፣ ማዕከሉ ቡናን ይበልጥ በጥራት ለማልማት የሚያበረታታ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ልማቱን በማስፋፋት ሰርተን ለመለዋጥ ብሎም ለሀገራችንም የውጭ ምንዛሪ ለማስገኘት ህግና ስርዓትን አክብረን እንድንሰራ ያደርጋል ብለዋል፡፡ ለተፈጥሮ ቡና ጣዕም ጥራትና ደረጃ መሻሻል ከማሳ ዝግጅት እስከ ምርት አሰባሰብ በግብርና ባለሙያዎች ሙያዊ ድጋፍ እያገኙ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በባሕርዳር ከተማ 24 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ
Dec 14, 2025 55
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 5/2018(ኢዜአ)፡- በባሕርዳር ከተማ ባለፉት አምስት ወራት 24 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 184 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ብርሃን ንጉሴ፤ የባሕርዳር ከተማን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል። ባለሃብቶች ወደ ከተማዋ መጥተው ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሳተፉ ባለፉት አምስት ወራት ጥረት ሲደረግ መቆየቱን አስረድተዋል። በዚህም 24 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 184 ባለሃብቶች አግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ሆቴልና ቱሪዝምን ጨምሮ በሌሎችም መስኮች ለመሰማራት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ጠይቀው እንደተሰጣቸው አስታወቀዋል። ባለሀብቶቹ ወደ ግንባታና ማምረት ስራ ሲሸጋገሩ ተኪና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ ለበርካታ ወገኖች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም ቀደም ሲል የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው በግንባታ ስራ ላይ ካሉ ፋብሪካዎች ባለፉት አምስት ወራት አምስቱ የማሽን ተከላ ስራቸውን አጠናቀው ወደማምረት ተግባር መግባታቸውን አንስተዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በማሽን ተከላ ስራ ላይ መሆናቸውን የጠቀሱት ኃላፊዋ፤ ፋብሪካዎቹ ፈጥነው የማሽን ተከላ ስራቸውን አጠናቀው ወደማምረት ስራ እንዲገቡ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። በማሽን ተከላ ላይ የሚገኙ ሁሉም ፋብሪካዎች ተጠናቀው ወደማምረት ተግባር ሲሸጋገሩ ተኪና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በብዛትና በጥራት ከማምረት ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እንዲፈጥሩና ለሀገሪቱ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አስተዋጽኦ በማበርከት ፋይዳቸው የጎላ ነው ብለዋል። በከተማዋ እስካሁን በማኒፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ 268 የተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች በማምረት ስራ ላይ እንደሚገኙ አውስተው፤ ኢንዱስትሪዎቹ በእንጨትና ብረታ ብረት፣ በምግብና ምግብ ነክ፣ በ" ጋርመንት እና ቴክስታይል " የስራ ዘርፎች የተሰማሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ከነዚህ ውስጥ 13 ኢንዱስትሪዎች ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርገው የተሰማሩ ሲሆን፤ በአጠቃላይ ከ11 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶችና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውን ከኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያው የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ኢትዮጵያ የቀጣናውን ትስስር የሚያጠናክሩ የልማትና የዘላቂ ሰላም ሥራዎችን እያከናወነች ነው
Dec 14, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና የኢኮኖሚ ትስስርን የሚያጠናክሩ የልማትና የዘላቂ ሰላም ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ በተለይም የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ለተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ተጋላጭ መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት በ2063 አጀንዳው የያዘውን ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ እንዲሁም የኢኮኖሚ ውህደት የመፍጠር ግብ እንዲሳካ ኢትዮጵያ በምትገኝበት ቀጣና መሪ ሚና እየተወጣች ነው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የዘርፉ ምሁራን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ አበክራ እየሰራች መሆኑን ተናግረዋል። የዓለም አቀፍ የውሃ ሕግ ተመራማሪው ከበደ ገርባ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት ከራሷ አልፋ ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እያደረገች ነው ብለዋል። በተለይም በቀጣናው የኢኮኖሚ ውህደት ለመፍጠር የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ወሳኝ መሆኑን አመልክተው፣ ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራትን በኤሌክትሪክ ኃይል እያስተሳሰረች መሆኑን ገልጸዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዲወጡ የነበራት ሚና ሊረሳ የማይችል ነው ብለዋል። በቀጣናው ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ የወሰደቻቸው እርምጃዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የተቸራቸው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በወዳጅነት መንፈስ ለጋራ ልማትና ዕድገት እየሰራች መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ ጥላሁን ተፈራ (ዶ/ር) ናቸው። በቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና ደህንነት ማስፈንን ጨምሮ ሁለንተናዊ ትብብርን ለማሳደግና በቀጣናው የጋራ ልማትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል። እንደ ባለሙያዎቹ ገለጻ፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሰላማዊ ግንኙነት የበለጠ በማሳደግ፣ የጋራ ልማትና ዕድገት ለማረጋገጥ ጥረቷን የበለጠ አጠናክራለች። የቀጣናው ህዝቦች የጋራ ማንነትና ተመሳሳይ እሴት ያላቸው መሆናቸውን ጠቅሰው፥ ሃብታቸውን በፍትሃዊነትና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ሊጠቀሙ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሃብትና አካባቢ ጥበቃ፣ የቴክኖሎጂ፣ የትምህርትና ስልጠና እንዲሁም የመሰረተ ልማት ግንባታ ስኬቶች ለቀጣናው ሀገራት ፋይዳቸው የላቀ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል እና አገልግሎቶቹን የማስፋት ሥራ እየተከናወነ ነው
Dec 14, 2025 35
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 5/2018(ኢዜአ)፡- መሶብ የአንድ ማዕከልንና የሚሰጡ የአገልግሎት ዓይነቶችን ለማስፋት እየተሠራ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሠመረ ጂራታ(ኢ/ር) ተናገሩ። ለዜጎች የሚሰጥ አገልግሎት ከቅሬታ የጸዳ፣ ጊዜና ወጭ ቆጣቢ፣ ፍትሐዊ ብሎም ተደራሽ እንዲሆን ማስቻል የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዓላማ መሆኑን አስገንዝበዋል። እንደ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአምሥት የክልል እና በሦስት የፌደራል ተቋማት በ33 ዘርፎች አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። እስካሁንም ከ6ሺህ 300 በላይ ተገልጋዮች አገልግሎት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል። በቀጣይ ወደ ማዕከሉ የሚገቡ ተቋማትና አገልግሎቶችን ቁጥር የማስፋት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህም መሠረት ተጨማሪ አንድ የፌደራል እና ሦስት የክልል ተቋማት ወደ መሶብ የአንድ ማዕከል መግባት የሚያስችላቸውን ሥራ እያከናወኑ ነው ብለዋል። ይህን ተከትሎም በአጭር ጊዜ አምሥት ተጨማሪ አገልግሎቶች ወደ ማዕከሉ እንደሚገቡ አመላክተዋል። በሌላ በኩል በአሶሳ ከተማ አሥተዳደር ደረጃ መሶብ የአንድ ማዕከል እንዲኖር እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በክልሉ የኮደርስ ስልጠና መርሐ ግብር በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ነው
Dec 13, 2025 121
ሚዛን አማን ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ):- የኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብር በተጠናከረና በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ አስታወቀ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ5 ሚሊዮን ዜጎች ነፃ የኮደርስ የስልጠና እድል በመመቻቸቱ እስካሁን በርካቶች የእድሉ ተጠቃሚ ሆነዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ምትኩ አስፋው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ 138 ሺህ ዜጎችን ለማሰልጠን ዕቅድ የተያዘ ሲሆን ከእነዚህም መካከል እስካሁን 16 ሺህ 700 የሚሆኑት ስልጠናውን አጠናቀው የምሥክር ወረቀት አግኝተዋል። በተያዘው ዓመትም የስልጠናው ሂደት ተጠናክሮ የቀጠለ በመሆኑ ተጨማሪ 63 ሺህ ዜጎችን የማሰልጠን እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የስልጠናው ዓላማ በዘርፉ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ማፍራት መሆኑን የተናገሩት ኃላፊው የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን ጊዜ ሳያባክኑ መመዝገብና መሰልጠን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። ሥልጠናውን ወስደው ሰርተፊኬት ከተቀበሉት መካከል የሲዝ ከተማ አስተዳደር ነዋሪው ወጣት ምናሉ ግዛቸው፤ በሥልጠናው ከዘመኑ ጋር ተወዳዳሪ እንድሆን የሚያስችለኝን እውቀት አግኝቻለሁ ብሏል። በወሰዳቸው አራት ኮርሶች ከመሠረታዊ የኮምፒዩተር እውቀት ጀምሮ አርተፊሻል ኢንተለጀንስ እና ፕሮግራሚንግ ላይ በቂ ክህሎት ማግኘቱን ተናግሯል። የሥልጠና አሰጣጥ ሁኔታው ቀላልና ለመያዝ ምቹ በመሆኑ ማንኛውም ሰው ጊዜ ብቻ ሰጥቶ ዕድሉን መጠቀም እንዳለበት ነው የተናገረው።
ሰልጣኞች በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀታቸው ዳብሯል
Dec 13, 2025 143
አርባምንጭ ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ):- የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የቴክኖሎጂ ዕውቀታቸውን እንዳዳበረው የአርባምንጭ ከተማ ሠልጣኞች ገለጹ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የአርባ ምንጭ ከተማ የኢትዮ-ኮደርስ ሰልጣኞች መካከል ወጣት ሊዲያ ዳሾ፤በአንድሮይድ ደቨሎፕመንት፣ ዳታ አናሊስስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስና ፕሮግራሚንግ ዘርፎች ስልጠና በመከታተል በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን የምስክር ወረቀት መውሰዷን ገልጻለች። ወቅቱ የሚጠይቀውን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዕውቀት መያዝ አስገዳጅ በመሆኑ ለዚሁ ራሷን ማብቃቷን አስረድታለች። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የኦን ላይን ሥራዎችን ለመወዳደርና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር ምቹ ሁኔታ ያለው መሆኑንም ተናግራለች፡፡ ሌላኛው ሠልጣኝ ወጣት ኦሳ ፋንታ በበኩሉ፤ በፕሮግራሚንግ እና ኮዲንግ ዘርፎች ስልጠና በመውሰድ የምስክር ወረቀት አግኝቷል። ስልጠናው ወቅቱን የዋጀ የቴክኖሎጂ ክህሎት በማላበስ አለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን እንደሚጨምርለት ተናግሯል። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መንግስት ወጪውን መሸፈኑ ዜጎችን ለማብቃትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ የታለመ ትልቅ ዕድል ነው ብሏል። የምስክር ወረቀቱ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው መሆኑ በየትኛውም ሀገር የሥራ እድልን ለማግኘት መሰረት እንደሚጥል ገልጿል። የአርባምንጭ ከተማ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ ሃላፊ አቶ በሃይሉ ካፒቴን ፤ መንግስት የዜጎችን የቴክኖሎጂ ዕውቀት ለማሳደግ የጀመረው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረጉን ተናግረዋል። በተለይ ለወጣቶች ዕውቀታቸውን በማሳደግ ለስራ ፈጠራ በማዋል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያሳድጉ የሚረዳ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና እንደ ሀገር ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በአርባምንጭ ከተማ 4 ሺህ 455 ዜጎች ስልጠና ወስደው የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም 4 ሺህ ዜጎችን ለማሠልጠን ግብ ተይዞ እየተሰራ ሲሆን በእስካሁኑ 2 ሺህ 829 ዜጎች መሠልጠናቸውን ገልጸዋል።
አዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግር አቅም ይሆናል
Dec 13, 2025 114
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ አዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግር አቅም እንደሚሆን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴዔታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠንካራ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን በመገንባት በእውቀትና ክህሎት የበቃ የሰው ኃይል ማፍራት የሚያስችል አዲስ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ስራ ላይ መዋሉ ይታወቃል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴዔታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ አዲሱ ስትራቴጂ የአረንጓዴ የክህሎት ልማት የስልጠና ፕሮግራሞችን የያዘ እና ለታዳሽ ኃይል ትኩረት የሰጠ ነው። ወደ አረንጓዴ ኢኮኖሚ በሚደረገው ሽግግር ብቃትና ክህሎት ያለው የሰው ኃይል ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ስትራቴጂው ብቃት ያለው እና ለአካባቢ ተስማሚ ቴክኖሎጂዎችን የሚተገብርና ሃብትን በቁጠባ የሚጠቀም ትውልድ ለመገንባት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ ሥርዓተ-ትምህርቶችን በአረንጓዴ የስራ መርሆዎችና አሠራሮች በማበልጸግ ተማሪዎች ከተቋማት ሲወጡ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ዘዴዎችንና መሣሪያዎችን እንዲጠቀሙ ያስችላል ብለዋል፡፡ አዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግር አቅም እንደሚሆንም ነው ሚኒስትር ዴዔታው የተናገሩት፡፡ በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ መሰረት የአረንጓዴ ቴክኒክና ሙያ ልጠና ፓኬጅ ተቀርጾ ወደ ስራ መግባቱን አመላክተዋል፡፡፡ ይህ ፓኬጅ ከብክለትና ከብክነት የጸዳ የሃይል አጠቃቀም እንዲኖር ያስችላል ብለዋል፡፡ በተቋማት ውስጥ ዘመናዊ እና ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ የማሰልጠኛ መሣሪያዎችን በማስገባት ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎች በንድፈ ሃሳብ ብቻ ሳይሆን በዘመናዊ አረንጓዴ ቴክኖሎጂዎች ተግባራዊ ልምምድ በማድረግ በሥራ ዓለም ውስጥ የአረንጓዴ ልምዶችን የመተግበር ብቃት እንዲኖራቸው እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ከዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ አዳዲስ የስራ ዕድሎችን መጠቀም እንደሚያስችልም እንዲሁ፡፡
ስፖርት
የኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ
Dec 14, 2025 46
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 5/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 12ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ ካደረጋቸው 11 ጨዋታዎች መካከል በ10ሩ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። 29 ግቦችን በጨዋታዎቹ ላይ ሲያስቆጥር ሰባት ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ30 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሊጉ ባካሄዳቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች ስምንቱን ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ አቻ ተለያይቷል። 27 ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ የተቆጠረበት አንድ ግብ ብቻ ነው። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ25 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ በርካታ ግቦችን ያስቆጠረ ቡድን ሲሆን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በበኩሉ በሊጉ ዝቅተኛ የግብ መጠን ያስተናገደ ቡድን ነው። በሊጉ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት ክለቦች ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ተጽእኖ ይኖረዋል። በሌላኛው መርሃ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከአዳማ ከተማ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ይጫወታሉ። ድሬዳዋ ከተማ በ12 ነጥብ ዘጠነኛ፣ አዳማ ከተማ በ14 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። ጨዋታው ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።
በኢትዮጵያ ዋንጫ ለሩብ ፍጻሜ የሚያልፉ ክለቦች የሚለዩባቸው ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ
Dec 14, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋንጫ ሶስተኛ ዙር የሁለተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በአዲስ አበባ ስታዲየም ደብረብርሃን ከተማ ከቤንች ማጂ ቡና ከቀኑ 7 ሰዓት እና ሲዳማ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ከ30 ላይ ይጫወታሉ። ሲዳማ ቡና አምና የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ እንደደነበር የሚታወስ ነው። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከንብ እግር ኳስ ክለብ ከቀኑ 7 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ትናንት በተደረጉ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ነጌሌ አርሲ፣ ቦዲቲ ከተማ፣ ኢትዮጵያ መድን እና መቻል ለሩብ ፍጻሜ አልፈዋል።
በፕሪሚየር ሊጉ ክሪስታል ፓላስ ከማንችስተር ሲቲ ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Dec 14, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 5/2018 (ኢዜአ):- የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ሁለተኛ ቀን ውሎ አምስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከቀኑ 11 ሰዓት ክሪስታል ፓላስ ከማንችስተር ሲቲ በሰልኸረስት ፓርክ ስታዲየም ይጫወታሉ። ክሪስታል ፓላስ በ26 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ማንችስተር ሲቲ በ31 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ቡድኖች በፕሪሚየር ሊጉ ሲገናኙ የአሁኑ ለ31ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 30 ጨዋታዎች ማንችስተር ሲቲ 19 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ክሪስታል ፓላስ አራት ጊዜ ሲያሸንፍ ሰባት ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። ማንችስተር ሲቲ በ30ዎቹ ጨዋታዎች 63 ጎሎችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ክሪስታል ፓላስ 30 ግቦችን አስቆጥሯል። ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች በነበራቸው ግንኙነት ማንችስተር ሲቲ ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ አቻ ወጥተዋል። በኦስትሪዊው ኦሊቨር ግላስነር የሚመራው ክሪስታል ፓላስ ጥሩ የውድድር ጊዜ በማሳለፍ ይገኛል። የፔፕ ጋርዲዮላው ማንችስተር ሲቲ ባለፈው ዓመት ከነበረው መጥፎ የውድድር ዓመት በኋላ ዘንድሮ ጠንካራ ግስጋሴ እያደረገ ነው። በፕሪሚየር ሊጉ ከምርጥ አራቱ ሁለቱ የሆኑት ክለቦች የሚያደርጉት ጨዋታ ጠንካራ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። ማንችስተር ሲቲ ካሸነፈ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ያደርጋል። የ39 ዓመቱ ዳረን ኢንግላንድ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ሰንደርላንድ ከኒውካስትል ዩናይትድ፣ ኖቲንግሃም ፎረስት ከቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ዌስትሃም ዩናይትድ ከአስቶንቪላ በተመሳሳይ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። ብሬንትፎርድ ከሊድስ ዩናይትድ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የሊጉ መሪ አርሰናል ዎልቭስን በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አገኘ
Dec 14, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 4/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አርሰናል ዎልቭስን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በኤምሬትስ ስታዲ በተካሄደው ጨዋታ በ70ኛው ደቂቃ ቡካዮ ሳካ ከማዕዘን ምት ያሻገረውን የዎልቭሱ ግብ ጠባቂ ሳም ጆንስተን በ70ኛው ደቂቃ በራሱ ላይ አስቆጥሮ አርሰናል መሪ ሆኗል። ቶሉ አርኮዳሬ በ90ኛው ደቂቃ ዎልቭስን አቻ አድርጓል። ጨዋታው በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ ሲባል ከ11 ወራት በኋላ ከጉዳት የተመለሰው ጋብርኤል ጄሱስ በ94ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ለአርሰናል ወሳኝ ድል አስገኝቷል። በጨዋታው አርሰናል ብልጫ ወስዶ ቢጫወትም በዎልቭስ የጥልቀት መከላከል የጨዋታ ስልት ፈተና አጋጥሞታል። በውድድር ዓመቱ 11ኛ ድሉን ያስመዘገበው የሊጉ መሪ አርሰናል ነጥቡን ወደ 36 ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ ብሏል። በአንጻሩ በሊጉ 14ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ዎልቭስ በሁለት ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ እስከ አሁን በሊጉ ምንም ጨዋታ አላሸነፈም። በሊጉ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንችስተር ሲቲ ነገ ከክሪስታል ፓላስ ጋር ከሜዳው ውጪ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል።
አካባቢ ጥበቃ
ኮፕ-32 ጉባኤን የበለጠ ስኬታማ ለማድረግ ባለሃብቶች ሚናቸውን መወጣት አለባቸው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Dec 12, 2025 206
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የምታስተናግደው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት (ኮፕ-32) ጉባኤን የበለጠ ስኬታማ ለማድረግ ባለሃብቶች ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ /ኮፕ-32/ በተመለከተ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በአራዳ ፓርክ ተካሂዷል። በመርሀ ግብሩ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሀይ ጳውሎስ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን፣ የመዲናዋ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የተለያዩ ባለብቶች እንዲሁም አልሚዎች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤን እንድታዘጋጅ የተመረጠችው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሳል የዲፕሎማሲ አመራር የተገኘ ስኬት ነው። ይህም ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል መሆኑን ነው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተናገሩት። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር፣ በከተሞች ልማትና ውበት የተመዘገቡ ውጤቶች ዓለም አቀፉን ጉባኤ እንድታስተናግድ ተመራጭ አድርጓታል ብለዋል። ኢትዮጵያ ብሎም አዲስ አበባ የዓለም የስበት ማዕከል መሆናቸውን በመጥቀስ፣ መዲናዋ ባለፈው ዓመት በርካታ ዓለም አቀፍ፣ አሕጉራዊ እና ሀገራዊ ሁነቶችን ማስተናገድ መቻሏን ገልጸዋል። ኮፕ-32 የዓለማችን ትልቁ የትኩረት ማዕከል መሆኑንም ነው የተናገሩት። ጉባኤው ለኢትዮጵያውያን ብዙ ዕድል ይዞ ይመጣል ያሉት ከንቲባዋ፤ ለዚህ ደግሞ መንግሥት የመሪነት ሚናውን እንዲወጣ ባለድርሻ አካላት በትብብር መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ በቀጣይ ሌሎች ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማዘጋጀት ዕድል እንድታገኝ፣ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ለማሳየትና የስራ ዕድል ለመፍጠር ወሳኝ ነው ብለዋል። በመሆኑም ባለሀብቶች አልሚዎችና አጠቃላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመንግሥት ጋር በመተባበር ጉባኤውን በስኬት ለማካሄድ ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው አስረድተዋል። ጉባኤውን በብቃት በማስተናገድ ለኢትዮጵያ ለውጥ መሰረት መጣል አለብን ያሉት ከንቲባዋ፤ ዛሬ የስራ ክፍፍል በማድረግና ዝግጅት በመጀመር ግባችንን ማሳካት አለብን ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሀይ ጳውሎስ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ አቅሟ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊና ሀገራዊ ኮንፍረንሶችን በብቃት ማስተናገድ የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ገልጸው፤ ውጤቱም በጋራ ትብብር የተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ሀገር ያስመዘገብናቸው ስኬቶች ለቀጣይ ስራዎቻችን መስፈንጠሪያ እንደሚሆኑ በመጥቀስ፤ ኮፕ-32 እንዲሁ የተገኘ አይደለም ብለዋል። ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤ አዘጋጅነትን ለማግኘት ዓለም አቀፋዊ ውድድር ማድረግ ነበረባት ያሉት ኃላፊዋ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ እና በሌሎችም አረንጓዴ ልማት ስራዎች በተገኙ ውጤቶች መመረጧን በመግለጽ። ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት አምስት ወራት ከ105 በላይ ሁነቶችን ማዘጋጀቷን ገልጸው፤ እነዚህ ስኬቶች የኮፕ 32 ጉባኤ ዝግጅትን በድል እንደምንወጣ የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉ ባለሃብቶችና አልሚዎች በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ኮፕ-32 ለማስተናገድ መመረጧ ትልቅ ዕድል ይዞ ይመጣል ብለዋል፡፡ በጉባኤው የሚሳተፉ አካላት የውጭ ምንዛሪ ይዘው እንደሚመጡ በማንሳት፤ በቆይታቸው የአገልግሎት ዘርፉን ገቢ ለማሳደግ ገንቢ ሚና እንደሚኖራቸው ገልጸዋል፡፡ ኮፕ-32 የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲያ ስኬት ማሳያ እንዲሁም ለገጽታ ግንባታ የጎላ አበርክቶ እንዳለውም ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ጉባኤውን በስኬት ማስተናገድ እንድትችል ከመንግስት ጎን በመሆን አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል፡፡ በብራዚል ቤለም በተካሄደው 30ኛ ጉባኤ ላይ ከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሄደውን 32ኛ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ (COP-32) ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል።
ኢትዮጵያ ኮፕ-32 ጉባኤን እንድታዘጋጅ መመረጧ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት ነው
Dec 12, 2025 132
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት(ኮፕ-32) ጉባኤን እንድታዘጋጅ መመረጥ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሳል የዲፕሎማሲ አመራር የተገኘ ስኬት መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ /ኮፕ-32/ በተመለከተ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በአራዳ ፓርክ ተካሂዷል። በመርሀ ግብሩ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሀይ ጳውሎስ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን፣ የመዲናዋ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የተለያዩ ባለሃብቶች እንዲሁም አልሚዎች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤን እንድታዘጋጅ የተመረጠችው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሳል የዲፕሎማሲ አመራር የተገኘ ስኬት ነው። ይህም ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል መሆኑን ነው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተናገሩት። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር፣ በከተሞች ልማትና ውበት የተመዘገቡ ውጤቶች ዓለም አቀፉን ጉባኤ እንድታስተናግድ ተመራጭ አድርጓታል ብለዋል። ኢትዮጵያ ብሎም አዲስ አበባ የዓለም የስበት ማዕከል መሆናቸውን በመጥቀስ፣ መዲናዋ ባለፈው ዓመት በርካታ ዓለም አቀፍ፣ አሕጉራዊ እና ሀገራዊ ሁነቶችን ማስተናገድ መቻሏን ገልጸዋል። ኮፕ-32 የዓለማችን ትልቁ የትኩረት ማዕከል መሆኑንም ነው የተናገሩት። ጉባኤው ለኢትዮጵያውያን ብዙ ዕድል ይዞ ይመጣል ያሉት ከንቲባዋ፤ ለዚህ ደግሞ መንግሥት የመሪነት ሚናውን እንዲወጣ ባለድርሻ አካላት በትብብር መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ በቀጣይ ሌሎች ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማዘጋጀት ዕድል እንድታገኝ፣ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ለማሳየትና የስራ ዕድል ለመፍጠር ወሳኝ ነው ብለዋል። በመሆኑም ባለሀብቶች አልሚዎችና አጠቃላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመንግሥት ጋር በመተባበር ጉባኤውን በስኬት ለማካሄድ ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው አስረድተዋል። ጉባኤውን በብቃት በማስተናገድ ለኢትዮጵያ ለውጥ መሰረት መጣል አለብን ያሉት ከንቲባዋ፤ ዛሬ የስራ ክፍፍል በማድረግና ዝግጅት በመጀመር ግባችንን ማሳካት አለብን ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሀይ ጳውሎስ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ አቅሟ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊና ሀገራዊ ኮንፍረንሶችን በብቃት ማስተናገድ የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ገልጸው፤ ውጤቱም በጋራ ትብብር የተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ሀገር ያስመዘገብናቸው ስኬቶች ለቀጣይ ስራዎቻችን መስፈንጠሪያ እንደሚሆኑ በመጥቀስ፤ ኮፕ-32 እንዲሁ የተገኘ አይደለም ብለዋል። ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤ አዘጋጅነትን ለማግኘት ዓለም አቀፋዊ ውድድር ማድረግ ነበረባት ያሉት ኃላፊዋ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ እና በሌሎችም አረንጓዴ ልማት ስራዎች በተገኙ ውጤቶች መመረጧን በመግለጽ። ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት አምስት ወራት ከ105 በላይ ሁነቶችን ማዘጋጀቷን ገልጸው፤ እነዚህ ስኬቶች የኮፕ 32 ጉባኤ ዝግጅትን በድል እንደምንወጣ የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። በብራዚል ቤለም በተካሄደው 30ኛው ጉባኤ ላይ ከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሄደውን 32ኛ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ(COP-32) ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ አንጻራዊ ጥንካሬ ይኖረዋል -የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
Dec 12, 2025 111
አዲስ አበባ ታህሳስ 3/2018 (ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መካከለኛው እና ደቡብ ደጋማ የአገሪቱ ክፍሎች የሌሌቱና የማለዳው ቅዝቃዜ አንጻራዊ ጥንካሬ እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ለኢዜአ በላከው መግለጫ የበጋው ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በአብዛኛዎቹ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ እንደሚስተዋል አስታውቋል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት በመነሳት ወደ አገራችን የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል። በአንዳንድ አካባቢዎች ቅዝቃዜው ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየሽ በታች እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ አስታውቋል። በዚህም በሰሜን ፣ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ፣ መካከለኛው እና ደቡብ ደጋማ የአገሪቱ ክፍሎች የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ አንጻራዊ ጥንካሬ እንደሚኖረው ገልጿል። አልፎ አልፎ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ውርጭ የማስከተል ጥንካሬ እንደሚኖረውም ጠቁሟል። በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የደቡብና ደቡብ ምስራቅ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ጥቂት ቦታዎች ቀላል መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ ብሏል። በተጨማሪም በሰሜን ምዕራብ፣ ምዕራብ እና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍሎች አልፎ አልፎ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የትንበያ መረጃዎች እንደሚያመላክቱ ገልጿል። በዚሁ ወቅት አብዛኛው ተፋሰሶች ደረቅ የአየር ሁኔታ እንደሚስተዋል አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል።
በክልሉ በመጪው ክረምት ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ችግኝ እየተዘጋጀ ነው
Dec 12, 2025 126
ባህርዳር ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በመጪው ክረምት ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ እየተዘጋጀ መሆኑ ተመላከተ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ እንደሀገር በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተራቁቱ መሬትን መልሶ በደን በመሸፈን እና የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ውሀ ሀብትን በማሳደግ ተጨባጭ ውጤት እያተመዘገበ ይገኛል። ባለፉት አመታት ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በትኩረት በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የክልሉን የደን ሽፋን ወደ 18 በመቶ ማሳደግ እንደተቻለም የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በተለያየ ምክንያት የተራቆተውን መሬት በደን መልሶ ለማልበስና የአየር ንብረት ሚዛኑን ለማስተካከል የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል። ተግባሩን ለማስቀጠልም በመጪው ክረምት ለሚተከሉ ችግኞች በመንግስት፣ በተቋማት፣ በማህበራትና በግል ተቋማት እንዲሁም ከ75 ሺህ በሚበልጡ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የተለያዩ ችግኞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል ብለዋል። እስካሁንም በ65 ሺህ 694 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ፣ ሀገር በቀልና የውጭ ዝርያ ችግኞችን ለማዘጋጀት የችግኝ መደቦችን በማዘጋጀት ዘር ማፍሰስ መቻሉን ገልጸዋል። ለአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተዘጋጁ ካሉት ችግኞችም 1 ነጥብ 7 ቢሊዮኑ በተራቆቱ፣ ለደን ተከላ በሚለዩና በበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ በሚከናወንባቸው ተፋሰሶች እንደሚተከሉም አስረድተዋል። በክልሉ ባለፈው የክረምት ወቅት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተተከለው ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መካከል በመጀመሪያ ዙር በተካሄደ ቆጠራ 86 ነጥብ 3 በመቶው ፀድቆ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝም ታውቋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 535
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል። በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 466
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 813
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 704
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል። ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል። ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ሐተታዎች
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 240
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 667
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል። የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 857
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 882
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው። በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው። የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል። በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 367
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2929
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2868
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3768
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2256
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1453
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7270
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5760
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 705
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው። እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም። የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል። የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል። ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!
ብልህ ከችግር ይማራል!!
Dec 2, 2025 457
ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል!! በማሙሽ ጋረደው ገራድ ተስፋዬ ተፈራ ትውልድና እድገታቸው በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ቃልሻ ቀበሌ ሲሆን በ1999 ዓ.ም በህገ ወጥ መንገድ ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው እንደነበር ያስታውሳሉ። ገንዘብ ለማግኘትና የመለውጥ ህልማቸውን ለማሳካት በሚል ሩቅ አስበው የጀመሩት ህገ ወጥ ጉዞ መዳረሻውን እስር ቤት አደረገው። ይህም ሁኔታ ''ሩቅ አሳቢ-ቅርብ አዳሪ'' አደረጋቸው። በባዕድ አገር በነበራቸው የ2 ዓመት የእስር ቤት ቆይታም የምግብ እጦትን ጨምሮ አካላዊ ጥቃትና ጉልበት ብዝበዛ እንዲሁም የተለያዩ ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶችን እንዳስተናገዱ ይናገራሉ። ይህም አልበቃ ብሎ ከአካባቢው በህገወጥ መንገድ የሚሰደዱ ወጣቶችን ጉልበት በመጠቀም ሰፋፊ እርሻዎች ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ የጉልበት ብዝበዛ ይፈፀምባቸው እንደነበርም ያስታውሳሉ። ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል! የሚሉት ገራድ ተስፋዬ ሩቅ ሳይጓዙ፣ ገንዘብ ሳያወጡ ሰርተው መለወጥ የሚችሉበትን አካባቢያቸውን ፀጋ ሳያማትሩ ስደት መሄዳቸው ቁጭት ፈጥሮባቸው ነበር፡፡ ይህም በሀገራቸው እንኳንስ የለማን መሬት ይቅርና የተቦረቦረ መሬትን አልምቶ ጉልበትንና ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል ከእስር ቤት ቆይታቸው ተምረው ከእስር እንደተፈቱም ወዲያውኑ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል። በ2001 ዓ.ም ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሱም በማህበር ተደራጅተው ከመንግሥት ባገኙት 70 ሺህ ብር ብድር በእንስሳት እርባታ ላይ ለመሰማራት 4 የወተት ከብቶችን ገዝተው የእርባታ ስራ መጀመራቸውን ይገልጻሉ፡፡ በዚህም የዞኑ አስተዳደር የሰጣቸውን መሬት አልምተው የእንስሳት እርባታውን አስፋፍተው መስራት ጀመሩ፡፡ አሁን ላይ የወተት ላሞቹን ቁጥር 37 በማድረስ የወተት ምርታማነታቸው አድጎ ከቤት ፍጆታ አልፎ ለሆሳዕና ከተማና አካባቢው በቀን ከ670 ሊትር በላይ ወተት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ለ40 ወጣቶችም ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ከመፍጠራቸውም ባሻገር የተለያዩ የጭነትና የስራ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራት መቻላቸውን ይናገራሉ። የጀመሩትን ስራ በጥምር ግብርና የማስፋትና የሚያገኙትን ወተት በማቀነባበር ምርቱን በተለያየ መልኩ ለገበያ የማቅረብ ራዕይን ሰንቀው በትጋት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በህገወጥ ስደት ካጋጠማቸው ችግር ተነስተው በተግባር ያዩትን ለሌሎች በማስተማር የስደትን አስከፊነት ለአካባቢያቸው ወጣቶች እያስገነዘቡ መሆኑን ገልጸዋል። ወጣቶች የስደትን አማራጭ ከመመልከታቸው በፊት የአካባቢያቸውን ፀጋ እንዲቃኙና ራዕይ ሰንቀው ራሳቸውን ለማሻሻል እንዲሰሩም መክረዋል። መለወጥ በውጪ ሀገር ብቻ ያለ የሚመስላቸው የቤተሰብ ኃላፊዎችም ልጆቻቸው በሀገራቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ በማመን ሊያግዟቸው እንደሚገባም አቶ ገራድ አስገንዝበዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደስላሴ፤ በክልሉ በርካታ ወጣቶች ያልተጨበጠ ተስፋ ሰንቀው ለህገወጥ ስደትና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ የሚያስችል አቅም በግብርናው ዘርፍ መኖሩን ጠቅሰው በዘርፉ የተሰማሩ ከስደት ተመላሾች በአካባቢያቸው ሰርተው ለስኬት እየበቁ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ላይ የሚገኙና የእነዚህን አካላት ተሞክሮ በመውሰድ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡