ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለተፈጥሯዊና ለሰው ሰራሽ ቅርሶች የሚደረግ ጥበቃን በጥናትና ምርምር እያገዘ ነው 
Apr 27, 2026 69
ሮቤ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ በባሌና ምሥራቅ ባሌ አካባቢ የሚገኙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ቅርሶች ለመጠበቅ በሚከናወኑ ተግባራት በጥናትና ምርምር እያገዘ መሆኑን መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው የድሬ ሼህ ሁሴን መካነ ቅርስን ከአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መጠበቅና መንከባከብ ዓላማ ያደረገ በትብብር የሚተገበር ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል።   የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክና ምርምር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው በተጓዳኝ የአካባቢው የቱሪዝም ሀብቶች እንዲለሙና እንዲተዋወቁ በጥናትና ምርምር እያገዘ ነው። አሁን ላይ ይፋ የተደረገው ፕሮጀክትም ቅርሶች በእድሜ በብዛት ለአደጋ እንዳይጋለጡ በጥናትና ምርምር የተደገፈ ጥበቃና እንክብካቤ እንዲሁም ጥገና ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ለመወጣት አላማ ያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።   ዩኒቨርሲቲው በባሌ፣ ምሥራቅ ባሌና ምዕራብ አርሲ ዞን አካባቢ የሚገኙ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ መስህቦች እንዲተዋወቁ እገዛ ከማድረግ ባሻገር በቅርሶቹ ላይ የሚደርሱ ተፅዕኖዎች እንዲቀረፉ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ ምርምሮችን እያካሄደ መሆኑን አመልክተዋል።   የምርምር ፕሮጄክቱ አባል ሀብታሙ ግዛው በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በቅርሶች ላይ የሚደርሱ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች በጥናት ተለይተው እንዲፈቱ ዓላማ ማድረጉን ተናግረዋል። በትብብር የሚሰራው ይሄው ፕሮጀክት በዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ምርምር በማካሄድ የመፍትሄ አማራጮችን እንደሚሰንድም አመልክተዋል። የለውጡ መንግስት ትኩረት ከሰጣቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች አንዱ ቱሪዝም ሲሆን በሀገሪቱ የቱሪስት መዳረሻዎችን የማስፋት፣ ቅርስን የመጠበቅና የመንከባከብ እንዲሁም መሰል ተግባራት በስፋትን እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል።
በግል ባለሀብት የሚለሙ የግብርና ስራዎች ለኢትዮጵያ የገጠር ሽግግር ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 
Apr 27, 2026 20
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የግል ባለሀብቶች በሶላር እና በከርሰ ምድር ውኃ በመጠቀም የሚያለሟቸው የግብርና ሥራዎች ለሀገሪቱ የገጠር ሽግግር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ዛሬ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሆሞሻ ወረዳ የሚገኘውን ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማትን በጎበኙበት ወቅት ነው። በዚህ እርሻ በ250 ሄክታር ላይ 27 ዓይነት የቋሚ ተክል፣ የሰብልና በፍጥነት ደራሽ የፍራፍሬ ልማት በተቀናጀ መልኩ እየተመረተ እንደሚገኝ በመልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል። ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት በኢትዮጵያ የግሉን ዘርፍ ያሳተፈ የግብርና ሥራ እንዲስፋፋ ለሚደረገው ሥራ አንድ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ በግል ባለሀብት እየለማ ያለው የግብርና ሥራ እንደ ሶላር ያሉ የኃይል አማራጮችን እና የከርሰ ምድር ውኃን በመጠቀም በመስኖ በማልማት ኢትዮጵያ ለጀመረችው የግብርና ልማት እና የገጠር ሽግግር ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ነው የገለጹት። ከተክል እና የሰብል ልማቱ ጎን ለጎንም የማር ምርት ላይ የሠጠው ትኩረት የአካባቢ እምቅ ፀጋ የመጠቀም ዕይታ በግሉ ዘርፍ እየሠረፀ መሆኑ የታየበት ነው ብለዋል። በእርሻው የዶሮ እርባታ፣ የንብ ማነብና የእንስሳት ልማት የተጀመረ ሲሆን የመኖ ዝግጅት መጀመሩም ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Apr 27, 2026 40
ሰመራ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ለዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል 18 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችና መድሃኒቶችን ዛሬ ድጋፍ አድርጓል። የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኀላፊ ዊቲካ ኖሬ በድጋፍ ርክክቡ ወቅት እንዳሉት ክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን እየተገበረ ነው። የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገለት የዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት ማዕከልም የዚሁ ትብብር ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል።   ቢሮው አዲስ ወደ ስራ ለገባው ማዕከል ከተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለእናቶችና ህፃናት ጤና መጠበቅ የሚያገለግሉ የህክምና ቁሳቁሶችን እያሟላ መሆኑንም አክለዋል። የዩኒሴፍ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ተወካይ ዶክተር መሐመድ ኢድሪስ የእናቶችና ህፃናት ጤናን ለመጠበቅ በሚደረገው ጥረት ድርጅቱ በትብብር እየሰራ ነው ብለዋል። አሁን ላይ ለዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት ማዕከል የተደረገው ድጋፍም የዚሁ ተግባር አካል መሆኑን ጠቅሰው ድጋፍም 18 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ዋጋ ያለው መሆኑን ገልፀዋል። የዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሁሴን ኡመር በበኩላቸው ሆስፒታሉ የህክምና አገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ በቅንጅት እየሰራ ነው። የዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት ማዕከል ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ተመርቆ ስራ መጀመሩ ይታወሳል።
ትውልዱ በቴክኒክና ሙያ ያገኘውን ክህሎት ለእድገት በተግባር መተርጎም ይጠበቅበታል
Apr 27, 2026 45
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ ትውልዱ በቴክኒክና ሙያ መስክ የሚያገኛቸውን ክህሎቶች በተግባር በመተርጎም ለእድገት የበኩሉን ሚና ሊጫወት እንደሚገባ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ገለጸ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ100ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዩቤልዩ በዓል የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት "ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ ለቀጣዩ ትውልድ" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ተከብሯል። በሥነ-ሥርዓቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮሌጁ መምህራንና ተማሪዎች፣ የቀድሞ ተማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በመድረኩ በኮሌጁ የተሰሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አውደ-ርዕይ፣ የኪነ-ጥበብ ስራዎችና የባህል አልባሳት ትዕይንት ቀርበዋል። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሚደቅሳ ከበደ በዚሁ ወቅት፤ የከተማ አስተዳደሩ የገበያውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ብቁ ሙያተኛ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ሰልጣኞች በቂ ክህሎት እንዲጨብጡ ከኢንዱስትሪዎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት ከቴክኖሎጂ ዕውቀት ውጪ ልማትና ዕድገት ማረጋገጥ እንደማይታሰብ ጠቁመው፤ በዚህ በኩል ተማሪዎች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በብቃት ሊወጡ ይገባል ብለዋል። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን ተሾመ ፈይሳ በበኩላቸው፤ ባለፉት አሥርት ዓመታት እንጦጦ በሚል ስያሜ ሲጠራ የቆየው ኮሌጅ፤ ዛሬ "ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" ተብሎ በይፋ የሚሰየምበት ዕለት በመሆኑ በዓሉን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል። በዓሉን ከማክበር ባለፈ በቴክኒክና ሙያ መስክ የታነፀ ትውልድ ለማፍራት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥልበት ነው ሲሉም ተናግረዋል። የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት ደጀኔ ተዘራ እንደተናገሩት፤ ማኅበሩ ኮሌጁን ለማጠናከር በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ነው። የስያሜው መስተካከል ከ100ኛ ዓመት በዓሉ ጋር መገጣጠሙ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን በበኩላቸው፤ ኮሌጁ ለሀገር ኩራት የሆኑ በርካታ ሙያተኞችን ማፍራቱን ተናግረዋል። በቀጣይም የካበተ ልምዱን ለሌሎች የሚያጋራበት ምቹ ሁኔታ ሊመቻች እንደሚገባም ጠቁመዋል። የአልማዝ ኢዩቤልዩ በዓሉ ከመጀመሪያው ጀምሮ እስከ መዝጊያው ሥነ-ሥርዓት ድረስ ስኬታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት ምስጋና ቀርቧል።
የአዲስ አበባ ስኬታማ የልማት ጉዞ የዜጎችን ተጠቃሚነትና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት እያረጋገጡ ነው
Apr 27, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ስኬታማ የልማት ጉዞ የዜጎችን ተጠቃሚነትና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት እያረጋገጡ መሆኑ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ። ከትናንት ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ሥራ አፈፃጸም ግምገማ ተጠናቋል። በዚሁ ወቅት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ በመዲናዋ ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ተሞክሮ የሚሆኑ የልማት ስኬቶች ተገኝተዋል ብለዋል።   የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶችም ሕብረብሔራዊ አንድነትን በማፅናት በዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ያመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢኮኖሚ መስክም ግዙፍ ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት በመገንባት የመዲናዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያንፁ ውጤታማ የልማት ስኬቶች መገኘታቸውን አስረድተዋል። የአዲስ አባባ አስደናቂ የልማት ስኬቶች የኢትዮጵያ የብልፅግና ተምሳሌት ከተማ የመገንባት ዕሳቤን በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። የመዲናዋ ዘርፈ ብዙ የልማት ስኬቶች የመዲናዋን ነዋሪዎች የአኗኗር ሥርዓትን በማዘመን ተጠቃሚነትን እያረጋገጡ መሆኑን አንስተዋል።
የሚታይ
የአዲስ አበባ ስኬታማ የልማት ጉዞ የዜጎችን ተጠቃሚነትና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት እያረጋገጡ ነው
Apr 27, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ስኬታማ የልማት ጉዞ የዜጎችን ተጠቃሚነትና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት እያረጋገጡ መሆኑ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ። ከትናንት ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ሥራ አፈፃጸም ግምገማ ተጠናቋል። በዚሁ ወቅት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ በመዲናዋ ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ተሞክሮ የሚሆኑ የልማት ስኬቶች ተገኝተዋል ብለዋል።   የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶችም ሕብረብሔራዊ አንድነትን በማፅናት በዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ያመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢኮኖሚ መስክም ግዙፍ ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት በመገንባት የመዲናዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያንፁ ውጤታማ የልማት ስኬቶች መገኘታቸውን አስረድተዋል። የአዲስ አባባ አስደናቂ የልማት ስኬቶች የኢትዮጵያ የብልፅግና ተምሳሌት ከተማ የመገንባት ዕሳቤን በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። የመዲናዋ ዘርፈ ብዙ የልማት ስኬቶች የመዲናዋን ነዋሪዎች የአኗኗር ሥርዓትን በማዘመን ተጠቃሚነትን እያረጋገጡ መሆኑን አንስተዋል።
የሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ የብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሙዚየምን ጎበኙ
Apr 27, 2026 90
‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19 /2018(ኢዜአ)፦ የሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ የብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሙዚየምን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ በሙዚየሙ የተደረገ ጥልቅ የታሪክ ጉዞ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የሞዛምቢክ ፕሬዝዳንት የሙዚየም ጉብኝት በኢትዮጵያ እያደረጉት ያለው ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አካል እንደሆነም ጠቁሟል። ጉብኝቱ የኢትዮጵያን ነፃና ጥንታዊ ሥልጣኔ የሚያሳይ መሆኑን የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፤ የሀገሪቱ ታሪክና ቅርሶችም ለታማኝና ባለርዕይ አጋርነቷ ህያው ምስክሮች መሆናቸውን አመልክቷል። ኢትዮጵያ ምድረ ቀደምት መሆኗን የሚያሳዩ ታሪካዊ ቅርሶቿን ስታጋራ፣ ጥንታዊ ጥንካሬዋ ለዘመናዊውና ለውጥን ለሚያረጋግጠው አጋርነቷ መሠረት መሆኑን በድጋሚ ማረጋገጧን ጽሕፈት ቤቱ ገልጿል። ጉብኝቱ አፍሪካውያን ወንድሞቻችን ለጋራ የወደፊት ዕጣ-ፈንታ በአንድነት ለመሥራት ወደ ሁለተኛ ቤታቸው እንዲመጡ ጥሪ የሚቀርብበት መሆኑንም አመልክቷል።
አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ ናቸው
Apr 27, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ላለፉት ሁለት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ዛሬ ተጠናቋል። የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብና አበባ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት በውጤታማነት መረጋገጥ ጀምረዋል። በግምገማው የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም የተታየ ሲሆን፤ በቀሪ ወራት የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት ማጠናቀቅ ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ የእቅድ አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባዋ፤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከተያዘው ዕቅድ ውስጥ በአጠቃላይ 96 በመቶ መፈጸም መቻሉን ተናግረዋል። በዚህም በሁሉም ዘርፎች አዲስ አበባን የኢትዮጵያ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን አብራርተዋል። በመዲናዋ የነዋሪውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ በተለይም በሰው ተኮር ተግባራት የዜጎችን ሕይወት ከመሠረቱ የቀየሩ በርካታ ፕሮጀክቶች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም ከመኖሪያ ቤቶች ግንባታ በተጨማሪ የምገባ ማዕከላት፣ የተማሪዎች ምገባ፣ የኮሪደር ልማትና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት ሕዝብን በማሳተፍ በተከናወኑ ተግባራት የመዲናዋን ሰላም አስተማማኝ ማድረግ መቻሉንም ነው ከንቲባዋ የገለጹት። አካባቢንና ወንዞችን ሲበክል የነበረውን የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት ለማሻሻል በተደረገው ጥረት፣ ቀደም ሲል አንድ ብቻ የነበረው የቆሻሻ ማጣሪያ ባለፉት አምስት ዓመታት ወደ 43 ማደጉን ጠቁመዋል። ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በፍጥነት የመጨረስ ባህል መዳበሩን ጠቅሰው፤ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ከተማ ከማድረግ አኳያ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆስፒታሎች መገንባታቸውንም ተናግረዋል። የአገልግሎት አሰጣጥን ከሌብነትና ከብልሹ አሠራር ለመከላከል በተከናወኑ ተግባራት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥን ማሳለጥ መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ የዋጋ ንረትን ከመከላከል አኳያም በከተማዋ የመግቢያ በሮች የገበያ ማዕከላት መገንባታቸውን ጠቅሰው፤ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች መስፋፋታቸውን ጠቁመዋል፡፡
በጋራ መከባበር ላይ ለተመሰረተ ዕድገትና ለውጥ ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ቤታቸው ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Apr 27, 2026 162
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በጋራ መከባበር ላይ ለተመሰረተ ዕድገትና ለውጥ ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ቤታቸው ናት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ወደ ኢትዮጵያ የእንኳን በደህና መጡ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የብዙ ጸጋዎች ባለቤት ሀገር እንደመሆኗ፤ አጋሮቿን ጸንቶ በቆየውና በጋራ መሰረቶች ላይ ማዕከል ባደረጉ የወል እድገትን ለማንበር ክንዶቿን ዘርግታ እንደምትቀበል ገልጸዋል።   አያይዘውም ከእውነተኛ አጋርነታችን የሚቀዳ፤ በጋራ መከባበር ላይ የተመሰረተ፣ በላቀ ርዕይ የተሞላ ዕድገትንና ለውጥን ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ መድረሻ ብቻ ሳትሆን፤ ሁለተኛ ቤታቸው ናት ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ቆይታ ለጋራ ስኬትና ለዘላቂ ወዳጅነት መሠረት የሚጥል ውጤታማ እንዲሆን ተመኝተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በጋራ መከባበር ላይ ለተመሰረተ ዕድገትና ለውጥ ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ቤታቸው ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Apr 27, 2026 162
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በጋራ መከባበር ላይ ለተመሰረተ ዕድገትና ለውጥ ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ቤታቸው ናት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ወደ ኢትዮጵያ የእንኳን በደህና መጡ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የብዙ ጸጋዎች ባለቤት ሀገር እንደመሆኗ፤ አጋሮቿን ጸንቶ በቆየውና በጋራ መሰረቶች ላይ ማዕከል ባደረጉ የወል እድገትን ለማንበር ክንዶቿን ዘርግታ እንደምትቀበል ገልጸዋል።   አያይዘውም ከእውነተኛ አጋርነታችን የሚቀዳ፤ በጋራ መከባበር ላይ የተመሰረተ፣ በላቀ ርዕይ የተሞላ ዕድገትንና ለውጥን ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ መድረሻ ብቻ ሳትሆን፤ ሁለተኛ ቤታቸው ናት ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ቆይታ ለጋራ ስኬትና ለዘላቂ ወዳጅነት መሠረት የሚጥል ውጤታማ እንዲሆን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ እና ሞዛምቢክ በወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ
Apr 27, 2026 386
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ሞዛምቢክ በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ጥምር ኮሚቴ በማቋቋም በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በሞዛምቢክ የመከላከያ ሚኒስትር በኢ-ክርስቲያቮ አርቱር ቹሜ የተመራውን ሉዑካን ቡድን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይታቸውም ሁለቱ ሀገራት በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።   እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጣር በ2009 በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደረገውን ወታደራዊ ግንኙነት መሰረት በማድረግም የጋራ ጥምር ኮሜቴ በማቋቋም ወደ ስራ መግባት በሚቻልባቸው መሰረታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል። በጋራ መስራት የበለጠ አቅም ለማግኘት እና በአጭር ጊዜ ውስጥ በዘርፉ ላይ ውጤት ለማምጣት እንደሚጠቅም በመድረኩ ላይ የተነሳ ሲሆን የዛሬው ውይይትም ጥምር ኮሚቴውን ለማቋቋምም ሆነ የወደፊቱን ወታደራዊ ግንኙነት እና ትብብር ለማስቀጠል የራሱን ሚና ይጫወታል መባሉን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የሰሜን ኮሪያ አምባሳደር ሲም ቶንግ ጎክ አሰናበቱ
Apr 27, 2026 394
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦‎ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የሰሜን ኮሪያ አምባሳደር ሲም ቶንግ ጎክን አሰናብተዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፤ አምባሳደር ሲም ቶንግ ጎክ በኢትዮጵያ ቆይታቸው የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት እንዲጠናከር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በኢትዮጵያና ሰሜን ኮሪያ መካከል በሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ታሪካዊ ወዳጅነት መኖሩንም ገልጸዋል። የሀገራቱን ታሪካዊ ወዳጅነት በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በቀጣይም ኢትዮጵያ የሀገራቱን የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ በመልዕክታቸው አምባሳደሩ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ላበረከቱት ሁሉ ምስጋናቸውን ገልፀው፤ ለወደፊቱ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ሚና በምርጫ ወቅት
Apr 26, 2026 2453
በኢዜአ ዐይን…! በዮሐንስ ደርበው የመገናኛ ብዙኃን ሚና በምርጫ ወቅት በአንድ ሀገር ምርጫ የመምረጥና የመመረጥ መብት መጎናጸፊያ፤ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ቁልፍ ሚና ይጫወታል።በሀገራችን ለ7ኛ ጊዜ ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫም የፊታችን ግንቦት 24 ጊዜ ተቆርጧል።ከዚህ ጋር ተያይዞም በምርጫ ሰሞን መገናኛ ብዙኃን የጎላ ሚና አላቸው ተብሎ ይጠበቃል።በዚህ ፅሁፍም ይህን ሚናቸውን እንቃኛለን። • መገናኛ ብዙኃን በምርጫ ወቅት አዘጋገብ ምን ይጠበቅባቸዋል? በምርጫ ወቅት መገናኛ ብዙኃን ትክክለኛ መረጃ ለሕብረተሰቡ በማድረስ ለሂደቱ ስኬታማነት፣ ተዓማኒነትና ተቀባይነት የማይተካ ሚና አላቸው።መገናኛ ብዙኃን ብሎም ጋዜጠኞች ሚናቸውን በአግባቡ ለመወጣት ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታን እና ዓለም አቀፋዊ ለውጦችን (ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ) ጉዳዮችን በውል ማጤን አለባቸው። መገናኛ ብዙኃን ገለልተኛ ሆነው ያዩትን፣የታዘቡትን ሙያዊ ሥነ-ምግባር በመከተል ለሕዝቡ መረጃዎችን እንዲያቀርቡ ይጠበቃል።በዚህ ሂደትም በጥብቅ ኃላፊነት ተግባራቸውን የማከናወን ግዴታ አለባቸው። በምርጫ ዘገባ ወቅት የመገናኛ ብዙኃን ዋነኛ ትኩረትና ሚናም፤ ነጻ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ አስፈላጊውን መረጃ ለሕዝቡ ማሻገር ነው። መገናኛ ብዙኃን ሲባልም፤በየጊዜው የሚወጣ ኅትመትን፣ የብሮድካስት አገልግሎትን እና የበይነመረብ መገናኛ ዐውታርን በመጠቀም መረጃዎቻቸውን ለሕዝብ ለማቅረብ የተቋቋሙ አካላት ማለት ነው። በምርጫ ወቅት የምርጫ ሂደትን ለመዘገብ (ለመከታተል) ዕውቅና (ፈቃድ) የተሰጠው የመገናኛ ብዙኃን (ጋዜጠኛ) ግዴታዎች እንዳሉበትም መገንዘብ ይገባል። ከእነዚህም መካከል፡- • የሕዝብን ሰብዓዊ መብትና መሠረታዊ ነጻነቶች ማክበር፤ • የምርጫ ቦርድን፣የምርጫ አስፈጻሚዎችን፣ የፀጥታና ደኅንነት እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት አካላትን ሚና እና ሥልጣን ማክበር፤ • ለምርጫ አስፈጻሚዎች ስለ ኃላፊነታቸው ምክር ወይም መመሪያ አለመስጠት፤ • መራጩ ድምፁን ለማን እንደሰጠ አለመጠየቅ፤ • የሕግ ጉዳዮችን በራስ አለመተርጐም እና የምርጫ ሂደትን የሚመለከት ሕጋዊ ያልሆነ መረጃ ወይም መመሪያ አለማስተላለፍ፤ • መራጭ በምሥጢር ድምፅ በሚሰጥበት ክፍል ወይም ለድምፅ መስጫ የተከለለ ቦታ ካሜራም ሆነ ሌላ የድምፅ ወይም የምስል መቅረጫ መሣሪያ አለመጠቀም፤ • ከአድልዎና ከወገንተኝነት በፀዳ ሁኔታ ተግባራትን ማከናወን፤ • የሀገሪቱን እና የአካባቢውን ባሕልና ልምድ ማክበር፤ • በቦርዱ የተሰጠውን የመታወቂያ ካርድ በሚታይ መልኩ በመያዝ መንቀሳቀስ፤ • የመራጭ ምዝገባ መረጃዎች በሠነድ ላይ ሲሰፍሩ ወይም መራጩ በድምፅ መስጫው ወረቀት ላይ የምርጫ ምልክት ሲያደርግ በፊልም አለመቅረፅ፤ፎቶግራፍም አለማንሳት፤ • የመራጮች ማንነትን ግላዊነት በሚነካ ሁኔታ የመራጮችን መዝገብ፣ የመራጮችን ምዝገባ መታወቂያ ወይም ማንኛውንም ተመሳሳይ ሠነድ በፊልም አለመቅረጽ፣ ፎቶግራፍ አለማንሳት ወይም ኮፒ አለማድረግ የሚሉት ይገኙበታል። በምርጫ ዘገባ ወቅት የመገናኛ ብዙኃን ዋነኛ ትኩረትና ሚናም፤ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ አስፈላጊውን መረጃ ለሕዝቡ ማድረስ ሲሆን፤ ለአብነትም እንዲያተኩሩባቸው ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል ቀጥሎ የተጠቀሱት ይገኙበታል፡- • ትክክለኛና ሚዛናዊ መረጃ ማቅረብ፡-መገናኛ ብዙኃን ማንኛውንም የፖለቲካ ፓርቲ ከመደገፍ ወይም ከማጥላላት ተቆጥበው ገለልተኛና ትክክለኛ መረጃ ለሕዝቡ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። • ለመራጮች ትምህርት (ወቅታዊ መረጃዎችን) መስጠት፡- ስለ ምርጫው ሂደት ዝርዝር ጉዳዮች ሕብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው ማድረግ ከመገናኛ ብዙኃን ይጠበቃል። በዚህም መሠረት ለአብነት፤ ስለ መራጮች ምዝገባ ሂደት (መቼ እንደሚጀመር፣ መቼ እንደሚጠናቀቅ፣ ምርጫው መቼ እንደሚካሄድ እና ስለ ድምጽ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት ለሕዝቡ ግንዛቤ መፍጠር) ዋነኛው ተግባራቸው ነው። • የሰላምና የአንድነት ግንባታ፡- በምርጫ ወቅት የሚነሱ ግጭቶችን ከማባባስ ይልቅ ሰላምን፣ ፍቅርንና አንድነትን የሚያጠናክሩ ዘገባዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ውይይቶችንና ክርክሮችን በማመቻቸት ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ምቹ መድረክ መፍጠርም አንዱ ሚናቸው ነው። • የሥነ-ምግባር ደንቦችን ማክበር፡- ጋዜጠኞችና የሚዲያ ተቋማት ከማንኛውም አካል የሚመጣባቸውን ጫና በመቋቋም፤ የጥቅም ግጭቶችን በማስወገድና ከጥላቻ ንግግሮች በመራቅ በሙያዊ ሥነ-ምግባር መመራት ይኖርባቸዋል። በአጠቃላይ መገናኛ ብዙኃን፤ ሕብረተሰቡ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጥ የማገዝ፣ ለፓርቲዎች የሐሳብ መድረክ የመፍጠር፣ መራጩን ሕዝብ የማሳወቅ (ማስተማር)፣ ትክክለኛ እና ሚዛናዊ መረጃ የማሠራጨት እንዲሁም ለቅድመ ምርጫ፣ ለምርጫ ወቅት እና ድኅረ ምርጫ ሰፊ ሽፋን እንዲሰጡ ይጠበቃል። በምርጫ ዘገባ መርሆዎች (ገለልተኝነት፣ ሚዛናዊነት፣ ትክክለኛነት፣ ፍትሐዊነት፣ ኃላፊነት) መሥራትም እንዲሁ። ጋዜጠኞችም፤ የዘገባ መርሆዎችን ማክበር፣ የተለያዩ ፓርቲዎችን ሐሳብ ማስተናገድ፣ ግልጽና የማያሻማ ቋንቋ መጠቀም፣ ፖሊሲና ማኒፌስቶ ላይ ማተኮር፣ አሳታፊና አካታች መሆን አለባቸው። በዚህ ሥራም የመረጃ ምንጮቻቸው፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግሥት አካላት ሊሆኑ ይገባል። በአጠቃላይ መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማነት የምርጫ ሕጉንና የመገናኛ ብዙኃን ዐዋጅን በተከተለ መልኩ በመዘገብ ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የዐቅም ግንባታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አስታውቋል። መገናኛ ብዙኃን በምርጫ ወቅት ሙያዊ ሥነ-ምግባርን የተከተለ አሳታፊና አካታች የሆነ ዘገባ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝቧል፡፡
ብዝኀ የኢኮኖሚ ዘርፎችን በመተግባር በገጠርም ሆነ  በከተማ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ ተችሏል
Apr 26, 2026 996
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡- ብዝኀ የኢኮኖሚ ዘርፎችን በመተግባር በገጠርም ሆነ በከተማ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ ተችሏል ሲሉ የድሬዳዋ አሥተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለጹ። በብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ በስፖርታዊ ውድድሮችና በድጋፍ ሰልፎች የታገዘ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል። በሳብያን የከተማ ወረዳ በተካሄደ ቅስቀሳ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ ከንቲባ ከድር ጁሃር እንዳሉት፤ ብልጽግና ፓርቲ ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ሰው ተኮር ልማቶችን ማሳካት ችሏል። ለዚህም ብዝኀ የኢኮኖሚ ዘርፎችን በመተግባር በገጠርም ሆነ በከተማ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን አንስተዋል። ፓርቲው የፖለቲካ እሳቤውን ኅብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ላይ በመመስረት የጋራ ትርክትን ለመገንባት በትኩረት መሥራቱንም አስረድተዋል። የተመዘገቡ ዘርፈ-ብዙ የልማትና የመልካም አሥተዳደር ውጤቶችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገርም ፓርቲው አበክሮ እንደሚሠራም አስገንዝበዋል። በገጠር ክላስተር በተካሄደው ቅስቀሳ ላይ የተሳተፉት የድሬዳዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሱልጣን አልይ ደግሞ፤ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በድሬዳዋ ገጠር ቀበሌዎች የልማት ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በመሠረተ-ልማት፣ በግብርና ዘርፍ፣ በጤናና በትምህርት የተመዘገቡ ውጤቶች የሕብረተሰብን ማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ችግሮች በከፍተኛ ደረጃ ማቃለላቸውን አስታውቀዋል። የገጠሩ ወጣት በተለያዩ የሥራ መስኮች በመሰማራት በኢኮኖሚ ራሱን ከመቻል ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል።
የለውጡ መንግሥት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት አረጋግጧል
Apr 26, 2026 1279
አሶሳ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግሥት የክልሉን የመልማት ዐቅም በማሳደግ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት አረጋግጧል ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሠ መሥተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ከዳር እስከ መሃል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የልማት ትንሳኤ" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሠ መሥተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የለውጡ መንግሥት የክልሉን የመልማት ዐቅም በማሳደግ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል። ከለውጡ በፊት ክልሉ የዳር ተመልካች በመሆኑ የመሠረተ-ልማት እጦት እና ኢፍትሐዊ የሀብት አጠቃቀም በመኖሩ የመልማት ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። ከለውጡ መንግሥት በኋላ በክልሉ አስተማማኝ ሰላም በመስፈኑ እና ፀጋዎቹን ለይቶ በማልማት ሕብረተሰቡ ከሀብቱ ተጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል።   በማዕድን ዘርፍ የታየው ለውጥ የኢኮኖሚ መሠረት በመሆኑ በስፋት እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የኮሪደር ልማት እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ውጤት መመዝገቡንም ገልጸዋል። ለውጡ የክልሉን የፖለቲካ ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ የፖለቲካ ምኅዳሩን በማስፋት በሀገር ጉዳይ ላይ ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ጠቅሰዋል።
ፖለቲካ
በጋራ መከባበር ላይ ለተመሰረተ ዕድገትና ለውጥ ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ቤታቸው ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Apr 27, 2026 162
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በጋራ መከባበር ላይ ለተመሰረተ ዕድገትና ለውጥ ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ቤታቸው ናት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ወደ ኢትዮጵያ የእንኳን በደህና መጡ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የብዙ ጸጋዎች ባለቤት ሀገር እንደመሆኗ፤ አጋሮቿን ጸንቶ በቆየውና በጋራ መሰረቶች ላይ ማዕከል ባደረጉ የወል እድገትን ለማንበር ክንዶቿን ዘርግታ እንደምትቀበል ገልጸዋል።   አያይዘውም ከእውነተኛ አጋርነታችን የሚቀዳ፤ በጋራ መከባበር ላይ የተመሰረተ፣ በላቀ ርዕይ የተሞላ ዕድገትንና ለውጥን ለሚሹ ሁሉ ኢትዮጵያ መድረሻ ብቻ ሳትሆን፤ ሁለተኛ ቤታቸው ናት ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ቆይታ ለጋራ ስኬትና ለዘላቂ ወዳጅነት መሠረት የሚጥል ውጤታማ እንዲሆን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ እና ሞዛምቢክ በወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ
Apr 27, 2026 386
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ሞዛምቢክ በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ጥምር ኮሚቴ በማቋቋም በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በሞዛምቢክ የመከላከያ ሚኒስትር በኢ-ክርስቲያቮ አርቱር ቹሜ የተመራውን ሉዑካን ቡድን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይታቸውም ሁለቱ ሀገራት በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።   እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጣር በ2009 በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደረገውን ወታደራዊ ግንኙነት መሰረት በማድረግም የጋራ ጥምር ኮሜቴ በማቋቋም ወደ ስራ መግባት በሚቻልባቸው መሰረታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል። በጋራ መስራት የበለጠ አቅም ለማግኘት እና በአጭር ጊዜ ውስጥ በዘርፉ ላይ ውጤት ለማምጣት እንደሚጠቅም በመድረኩ ላይ የተነሳ ሲሆን የዛሬው ውይይትም ጥምር ኮሚቴውን ለማቋቋምም ሆነ የወደፊቱን ወታደራዊ ግንኙነት እና ትብብር ለማስቀጠል የራሱን ሚና ይጫወታል መባሉን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የሰሜን ኮሪያ አምባሳደር ሲም ቶንግ ጎክ አሰናበቱ
Apr 27, 2026 394
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦‎ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የሰሜን ኮሪያ አምባሳደር ሲም ቶንግ ጎክን አሰናብተዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፤ አምባሳደር ሲም ቶንግ ጎክ በኢትዮጵያ ቆይታቸው የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት እንዲጠናከር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በኢትዮጵያና ሰሜን ኮሪያ መካከል በሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ታሪካዊ ወዳጅነት መኖሩንም ገልጸዋል። የሀገራቱን ታሪካዊ ወዳጅነት በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በቀጣይም ኢትዮጵያ የሀገራቱን የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ በመልዕክታቸው አምባሳደሩ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ላበረከቱት ሁሉ ምስጋናቸውን ገልፀው፤ ለወደፊቱ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ሚና በምርጫ ወቅት
Apr 26, 2026 2453
በኢዜአ ዐይን…! በዮሐንስ ደርበው የመገናኛ ብዙኃን ሚና በምርጫ ወቅት በአንድ ሀገር ምርጫ የመምረጥና የመመረጥ መብት መጎናጸፊያ፤ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ቁልፍ ሚና ይጫወታል።በሀገራችን ለ7ኛ ጊዜ ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫም የፊታችን ግንቦት 24 ጊዜ ተቆርጧል።ከዚህ ጋር ተያይዞም በምርጫ ሰሞን መገናኛ ብዙኃን የጎላ ሚና አላቸው ተብሎ ይጠበቃል።በዚህ ፅሁፍም ይህን ሚናቸውን እንቃኛለን። • መገናኛ ብዙኃን በምርጫ ወቅት አዘጋገብ ምን ይጠበቅባቸዋል? በምርጫ ወቅት መገናኛ ብዙኃን ትክክለኛ መረጃ ለሕብረተሰቡ በማድረስ ለሂደቱ ስኬታማነት፣ ተዓማኒነትና ተቀባይነት የማይተካ ሚና አላቸው።መገናኛ ብዙኃን ብሎም ጋዜጠኞች ሚናቸውን በአግባቡ ለመወጣት ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታን እና ዓለም አቀፋዊ ለውጦችን (ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ) ጉዳዮችን በውል ማጤን አለባቸው። መገናኛ ብዙኃን ገለልተኛ ሆነው ያዩትን፣የታዘቡትን ሙያዊ ሥነ-ምግባር በመከተል ለሕዝቡ መረጃዎችን እንዲያቀርቡ ይጠበቃል።በዚህ ሂደትም በጥብቅ ኃላፊነት ተግባራቸውን የማከናወን ግዴታ አለባቸው። በምርጫ ዘገባ ወቅት የመገናኛ ብዙኃን ዋነኛ ትኩረትና ሚናም፤ ነጻ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ አስፈላጊውን መረጃ ለሕዝቡ ማሻገር ነው። መገናኛ ብዙኃን ሲባልም፤በየጊዜው የሚወጣ ኅትመትን፣ የብሮድካስት አገልግሎትን እና የበይነመረብ መገናኛ ዐውታርን በመጠቀም መረጃዎቻቸውን ለሕዝብ ለማቅረብ የተቋቋሙ አካላት ማለት ነው። በምርጫ ወቅት የምርጫ ሂደትን ለመዘገብ (ለመከታተል) ዕውቅና (ፈቃድ) የተሰጠው የመገናኛ ብዙኃን (ጋዜጠኛ) ግዴታዎች እንዳሉበትም መገንዘብ ይገባል። ከእነዚህም መካከል፡- • የሕዝብን ሰብዓዊ መብትና መሠረታዊ ነጻነቶች ማክበር፤ • የምርጫ ቦርድን፣የምርጫ አስፈጻሚዎችን፣ የፀጥታና ደኅንነት እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት አካላትን ሚና እና ሥልጣን ማክበር፤ • ለምርጫ አስፈጻሚዎች ስለ ኃላፊነታቸው ምክር ወይም መመሪያ አለመስጠት፤ • መራጩ ድምፁን ለማን እንደሰጠ አለመጠየቅ፤ • የሕግ ጉዳዮችን በራስ አለመተርጐም እና የምርጫ ሂደትን የሚመለከት ሕጋዊ ያልሆነ መረጃ ወይም መመሪያ አለማስተላለፍ፤ • መራጭ በምሥጢር ድምፅ በሚሰጥበት ክፍል ወይም ለድምፅ መስጫ የተከለለ ቦታ ካሜራም ሆነ ሌላ የድምፅ ወይም የምስል መቅረጫ መሣሪያ አለመጠቀም፤ • ከአድልዎና ከወገንተኝነት በፀዳ ሁኔታ ተግባራትን ማከናወን፤ • የሀገሪቱን እና የአካባቢውን ባሕልና ልምድ ማክበር፤ • በቦርዱ የተሰጠውን የመታወቂያ ካርድ በሚታይ መልኩ በመያዝ መንቀሳቀስ፤ • የመራጭ ምዝገባ መረጃዎች በሠነድ ላይ ሲሰፍሩ ወይም መራጩ በድምፅ መስጫው ወረቀት ላይ የምርጫ ምልክት ሲያደርግ በፊልም አለመቅረፅ፤ፎቶግራፍም አለማንሳት፤ • የመራጮች ማንነትን ግላዊነት በሚነካ ሁኔታ የመራጮችን መዝገብ፣ የመራጮችን ምዝገባ መታወቂያ ወይም ማንኛውንም ተመሳሳይ ሠነድ በፊልም አለመቅረጽ፣ ፎቶግራፍ አለማንሳት ወይም ኮፒ አለማድረግ የሚሉት ይገኙበታል። በምርጫ ዘገባ ወቅት የመገናኛ ብዙኃን ዋነኛ ትኩረትና ሚናም፤ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ አስፈላጊውን መረጃ ለሕዝቡ ማድረስ ሲሆን፤ ለአብነትም እንዲያተኩሩባቸው ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል ቀጥሎ የተጠቀሱት ይገኙበታል፡- • ትክክለኛና ሚዛናዊ መረጃ ማቅረብ፡-መገናኛ ብዙኃን ማንኛውንም የፖለቲካ ፓርቲ ከመደገፍ ወይም ከማጥላላት ተቆጥበው ገለልተኛና ትክክለኛ መረጃ ለሕዝቡ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። • ለመራጮች ትምህርት (ወቅታዊ መረጃዎችን) መስጠት፡- ስለ ምርጫው ሂደት ዝርዝር ጉዳዮች ሕብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው ማድረግ ከመገናኛ ብዙኃን ይጠበቃል። በዚህም መሠረት ለአብነት፤ ስለ መራጮች ምዝገባ ሂደት (መቼ እንደሚጀመር፣ መቼ እንደሚጠናቀቅ፣ ምርጫው መቼ እንደሚካሄድ እና ስለ ድምጽ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት ለሕዝቡ ግንዛቤ መፍጠር) ዋነኛው ተግባራቸው ነው። • የሰላምና የአንድነት ግንባታ፡- በምርጫ ወቅት የሚነሱ ግጭቶችን ከማባባስ ይልቅ ሰላምን፣ ፍቅርንና አንድነትን የሚያጠናክሩ ዘገባዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ውይይቶችንና ክርክሮችን በማመቻቸት ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ምቹ መድረክ መፍጠርም አንዱ ሚናቸው ነው። • የሥነ-ምግባር ደንቦችን ማክበር፡- ጋዜጠኞችና የሚዲያ ተቋማት ከማንኛውም አካል የሚመጣባቸውን ጫና በመቋቋም፤ የጥቅም ግጭቶችን በማስወገድና ከጥላቻ ንግግሮች በመራቅ በሙያዊ ሥነ-ምግባር መመራት ይኖርባቸዋል። በአጠቃላይ መገናኛ ብዙኃን፤ ሕብረተሰቡ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጥ የማገዝ፣ ለፓርቲዎች የሐሳብ መድረክ የመፍጠር፣ መራጩን ሕዝብ የማሳወቅ (ማስተማር)፣ ትክክለኛ እና ሚዛናዊ መረጃ የማሠራጨት እንዲሁም ለቅድመ ምርጫ፣ ለምርጫ ወቅት እና ድኅረ ምርጫ ሰፊ ሽፋን እንዲሰጡ ይጠበቃል። በምርጫ ዘገባ መርሆዎች (ገለልተኝነት፣ ሚዛናዊነት፣ ትክክለኛነት፣ ፍትሐዊነት፣ ኃላፊነት) መሥራትም እንዲሁ። ጋዜጠኞችም፤ የዘገባ መርሆዎችን ማክበር፣ የተለያዩ ፓርቲዎችን ሐሳብ ማስተናገድ፣ ግልጽና የማያሻማ ቋንቋ መጠቀም፣ ፖሊሲና ማኒፌስቶ ላይ ማተኮር፣ አሳታፊና አካታች መሆን አለባቸው። በዚህ ሥራም የመረጃ ምንጮቻቸው፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግሥት አካላት ሊሆኑ ይገባል። በአጠቃላይ መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማነት የምርጫ ሕጉንና የመገናኛ ብዙኃን ዐዋጅን በተከተለ መልኩ በመዘገብ ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የዐቅም ግንባታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አስታውቋል። መገናኛ ብዙኃን በምርጫ ወቅት ሙያዊ ሥነ-ምግባርን የተከተለ አሳታፊና አካታች የሆነ ዘገባ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝቧል፡፡
ብዝኀ የኢኮኖሚ ዘርፎችን በመተግባር በገጠርም ሆነ  በከተማ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ ተችሏል
Apr 26, 2026 996
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡- ብዝኀ የኢኮኖሚ ዘርፎችን በመተግባር በገጠርም ሆነ በከተማ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ ተችሏል ሲሉ የድሬዳዋ አሥተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለጹ። በብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ በስፖርታዊ ውድድሮችና በድጋፍ ሰልፎች የታገዘ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል። በሳብያን የከተማ ወረዳ በተካሄደ ቅስቀሳ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ ከንቲባ ከድር ጁሃር እንዳሉት፤ ብልጽግና ፓርቲ ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ሰው ተኮር ልማቶችን ማሳካት ችሏል። ለዚህም ብዝኀ የኢኮኖሚ ዘርፎችን በመተግባር በገጠርም ሆነ በከተማ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን አንስተዋል። ፓርቲው የፖለቲካ እሳቤውን ኅብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ላይ በመመስረት የጋራ ትርክትን ለመገንባት በትኩረት መሥራቱንም አስረድተዋል። የተመዘገቡ ዘርፈ-ብዙ የልማትና የመልካም አሥተዳደር ውጤቶችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገርም ፓርቲው አበክሮ እንደሚሠራም አስገንዝበዋል። በገጠር ክላስተር በተካሄደው ቅስቀሳ ላይ የተሳተፉት የድሬዳዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሱልጣን አልይ ደግሞ፤ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በድሬዳዋ ገጠር ቀበሌዎች የልማት ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በመሠረተ-ልማት፣ በግብርና ዘርፍ፣ በጤናና በትምህርት የተመዘገቡ ውጤቶች የሕብረተሰብን ማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ችግሮች በከፍተኛ ደረጃ ማቃለላቸውን አስታውቀዋል። የገጠሩ ወጣት በተለያዩ የሥራ መስኮች በመሰማራት በኢኮኖሚ ራሱን ከመቻል ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል።
የለውጡ መንግሥት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት አረጋግጧል
Apr 26, 2026 1279
አሶሳ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግሥት የክልሉን የመልማት ዐቅም በማሳደግ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት አረጋግጧል ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሠ መሥተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ከዳር እስከ መሃል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የልማት ትንሳኤ" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል።   ርዕሠ መሥተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የለውጡ መንግሥት የክልሉን የመልማት ዐቅም በማሳደግ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል። ከለውጡ በፊት ክልሉ የዳር ተመልካች በመሆኑ የመሠረተ-ልማት እጦት እና ኢፍትሐዊ የሀብት አጠቃቀም በመኖሩ የመልማት ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። ከለውጡ መንግሥት በኋላ በክልሉ አስተማማኝ ሰላም በመስፈኑ እና ፀጋዎቹን ለይቶ በማልማት ሕብረተሰቡ ከሀብቱ ተጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል።   በማዕድን ዘርፍ የታየው ለውጥ የኢኮኖሚ መሠረት በመሆኑ በስፋት እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የኮሪደር ልማት እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ውጤት መመዝገቡንም ገልጸዋል። ለውጡ የክልሉን የፖለቲካ ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ የፖለቲካ ምኅዳሩን በማስፋት በሀገር ጉዳይ ላይ ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ጠቅሰዋል።
ማህበራዊ
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለተፈጥሯዊና ለሰው ሰራሽ ቅርሶች የሚደረግ ጥበቃን በጥናትና ምርምር እያገዘ ነው 
Apr 27, 2026 69
ሮቤ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ በባሌና ምሥራቅ ባሌ አካባቢ የሚገኙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ቅርሶች ለመጠበቅ በሚከናወኑ ተግባራት በጥናትና ምርምር እያገዘ መሆኑን መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው የድሬ ሼህ ሁሴን መካነ ቅርስን ከአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መጠበቅና መንከባከብ ዓላማ ያደረገ በትብብር የሚተገበር ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል።   የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክና ምርምር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው በተጓዳኝ የአካባቢው የቱሪዝም ሀብቶች እንዲለሙና እንዲተዋወቁ በጥናትና ምርምር እያገዘ ነው። አሁን ላይ ይፋ የተደረገው ፕሮጀክትም ቅርሶች በእድሜ በብዛት ለአደጋ እንዳይጋለጡ በጥናትና ምርምር የተደገፈ ጥበቃና እንክብካቤ እንዲሁም ጥገና ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ለመወጣት አላማ ያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።   ዩኒቨርሲቲው በባሌ፣ ምሥራቅ ባሌና ምዕራብ አርሲ ዞን አካባቢ የሚገኙ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ መስህቦች እንዲተዋወቁ እገዛ ከማድረግ ባሻገር በቅርሶቹ ላይ የሚደርሱ ተፅዕኖዎች እንዲቀረፉ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ ምርምሮችን እያካሄደ መሆኑን አመልክተዋል።   የምርምር ፕሮጄክቱ አባል ሀብታሙ ግዛው በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በቅርሶች ላይ የሚደርሱ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች በጥናት ተለይተው እንዲፈቱ ዓላማ ማድረጉን ተናግረዋል። በትብብር የሚሰራው ይሄው ፕሮጀክት በዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ምርምር በማካሄድ የመፍትሄ አማራጮችን እንደሚሰንድም አመልክተዋል። የለውጡ መንግስት ትኩረት ከሰጣቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች አንዱ ቱሪዝም ሲሆን በሀገሪቱ የቱሪስት መዳረሻዎችን የማስፋት፣ ቅርስን የመጠበቅና የመንከባከብ እንዲሁም መሰል ተግባራት በስፋትን እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል።
በክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Apr 27, 2026 40
ሰመራ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ለዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል 18 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችና መድሃኒቶችን ዛሬ ድጋፍ አድርጓል። የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኀላፊ ዊቲካ ኖሬ በድጋፍ ርክክቡ ወቅት እንዳሉት ክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን እየተገበረ ነው። የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገለት የዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት ማዕከልም የዚሁ ትብብር ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል።   ቢሮው አዲስ ወደ ስራ ለገባው ማዕከል ከተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለእናቶችና ህፃናት ጤና መጠበቅ የሚያገለግሉ የህክምና ቁሳቁሶችን እያሟላ መሆኑንም አክለዋል። የዩኒሴፍ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ተወካይ ዶክተር መሐመድ ኢድሪስ የእናቶችና ህፃናት ጤናን ለመጠበቅ በሚደረገው ጥረት ድርጅቱ በትብብር እየሰራ ነው ብለዋል። አሁን ላይ ለዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት ማዕከል የተደረገው ድጋፍም የዚሁ ተግባር አካል መሆኑን ጠቅሰው ድጋፍም 18 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ዋጋ ያለው መሆኑን ገልፀዋል። የዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሁሴን ኡመር በበኩላቸው ሆስፒታሉ የህክምና አገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ በቅንጅት እየሰራ ነው። የዱብቲ አጠቃላይ ሆስፒታል የእናቶችና ህፃናት ማዕከል ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ተመርቆ ስራ መጀመሩ ይታወሳል።
የመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ በዕድገት ጉዞ ውስጥ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ኃላፊነት እንዲሰፍን ያስችላል
Apr 27, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ የመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ በዕድገት ጉዞ ውስጥ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ኃላፊነት እንዲሰፍን እንደሚያስችል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። ቋሚ ኮሚቴው በመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ ላይ የአስረጂ መድረክ አካሂዷል።   የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕንባ ጠባቂ ወይዘሮ ስመኝ ውቤ በዚሁ ወቅት በረቂቅ አዋጁ የተካተቱ ዋና ዋና ነጥቦችን አብራርተዋል። የተፈፃሚነት ወሰንን በተመለከተ መንግስት ነክ ስራ ላይ የተሰማራ ወይም መንግስት በንግድ ማህበር ድርሻ ወይም አክሲዮን ያለው ንግድ ማህበር በረቂቅ አዋጁ እንዲሸፈን መደረጉን ጠቅሰዋል።   መረጃ የማግኘት መብት የሚገደብባቸው ልዩ ሁኔታዎች ከዓለም አቀፍ ሕጎችና ከአፍሪካ ሞዴል የመረጃ ነጻነት ሕግ ጋር እንዲጣጣሙ ተደርገው በግልጽ መቀመጡንም ተናግረዋል። ዜጎችና የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በአጭር ጊዜ እና በቀላሉ መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችልና የሚያበረታታ የተሳለጠ የመረጃ ተደራሽነት እንዲሰፍን የሚያደርግ ስርዓት መዘርጋቱን ገልጸዋል። ከልካይ ያልሆኑ የክፍያ ስርዓት መካተቱንና ለመረጃ ሰጪዎች ህጋዊ ጥበቃ ማድረጉን አብራርተዋል። የተጠየቀ መረጃ በሚከለከልበት ጊዜ ቀደም ሲል ይወስድ የነበረው ረጅም የይግባኝ ጊዜ በረቂቅ አዋጁ እንዲያጥር ተደርጓል ብለዋል። የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የአዋጁን አፈጻጸም በአግባቡ መከታተል እንዲችል በቂ ሥልጣንና ተቋማዊ አደረጃጀት እንዲኖረው የሚያስችሉ ዝርዝር ድንጋጌዎች ተካተዋል።   የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ፤ ማሻሻያው በመንግስት፣ በዜጎች እና በባለድርሻ አካላት መካከል በሚከናወነው የዕደገት ጉዞ ውስጥ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት እና ኃላፊነት እንዲሰፍን የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ረቂቅ አዋጅ የተደራጀና ጠንካራ አሰራርን በመዘርጋት ዜጎች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡና ተጠያቂነት እንዲሰፍን የሚያስችሉ የተሟሉ ድንጋጌዎችን የያዘ መሆኑንም አስረድተዋል። የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ በሰጡት ማጠቃለያ፤ አዋጁን ማሻሻል ያስፈለገው ካለው ወቅታዊ ለውጥ እና አዳዲስ ሁኔታዎች አኳያ ተገቢ በመሆኑ ነው ብለዋል። ከዚህ ቀደም የነበሩ መሠረታዊ ጉዳዮችን በአግባቡ መለየት እንደሚገባ ጠቁመው፤ በተለይም በትርጓሜ አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት አሳስበዋል። በተጨማሪም የማሻሻያ ሥራውን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የሌሎች ሀገራት ተሞክሮዎችን ማየትና መቅሰም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዞኑ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት ተከናውነዋል 
Apr 27, 2026 111
ጎንደር ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ማሕበረሰቡ ባደረገው ከ114 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ኃላፊ አቶ ክንዱ ዘውዱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ህብረተሰቡን በንቅናቄ በማሳተፍ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በትኩረት ተሰርቷል። በዚህም ከ400 በላይ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን ገንብቶ ለአገልግሎት በማብቃት ከ16 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።   በተጨማሪም 18 ቤተ መጻህፍት፣ 923 መጸዳጃ ቤቶችና 1 ሺህ 300 የመጠጥ ውሃ ተቋማት በማስገንባት ተማሪዎች የተሟላ አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በተለይም 222 የመምህራን መኖሪያ ቤቶችን በማስገንባት ተረጋግተው የመማር ማስተማር ስራውን ለማቀላጠፍ እንዲችሉ መደረጉንም አስረድተዋል። የአማራ ልማት ማህበርም ስድስት የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ማስጀመሩን ነው የጠቆሙት። የትምህርት ሚኒስቴርም እንዲሁ 15 የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለማስጀመር የተቋራጭ ልየታ እያካሔደ መሆኑን አብራርተዋል። በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆችም በቆላድባ፣ በጭልጋና በወገራ ወረዳዎች ሶስት ትምህርት ቤቶችን እያስገነቡ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡   ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችና የመምህራን መጠለያዎች በህብረተሰቡ ድጋፍ መሰራታቸውን የተናገሩት በወገራ ወረዳ የኮሶዬ ትምህርት ቤት የወላጅ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ሰጠኝ ታከለ ናቸው፡፡ በምእራብ ደንቢያ ወረዳ የጯሂት ከተማ ነዋሪ አቶ ተስፉ ባዩ በበኩላቸው፤ በንቅናቄው ህብረተሰቡ የሚያደርገው ድጋፍ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እያገዘ ነው ብለዋል፡፡
ኢኮኖሚ
በግል ባለሀብት የሚለሙ የግብርና ስራዎች ለኢትዮጵያ የገጠር ሽግግር ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 
Apr 27, 2026 20
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የግል ባለሀብቶች በሶላር እና በከርሰ ምድር ውኃ በመጠቀም የሚያለሟቸው የግብርና ሥራዎች ለሀገሪቱ የገጠር ሽግግር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ዛሬ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሆሞሻ ወረዳ የሚገኘውን ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማትን በጎበኙበት ወቅት ነው። በዚህ እርሻ በ250 ሄክታር ላይ 27 ዓይነት የቋሚ ተክል፣ የሰብልና በፍጥነት ደራሽ የፍራፍሬ ልማት በተቀናጀ መልኩ እየተመረተ እንደሚገኝ በመልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል። ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት በኢትዮጵያ የግሉን ዘርፍ ያሳተፈ የግብርና ሥራ እንዲስፋፋ ለሚደረገው ሥራ አንድ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ በግል ባለሀብት እየለማ ያለው የግብርና ሥራ እንደ ሶላር ያሉ የኃይል አማራጮችን እና የከርሰ ምድር ውኃን በመጠቀም በመስኖ በማልማት ኢትዮጵያ ለጀመረችው የግብርና ልማት እና የገጠር ሽግግር ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ነው የገለጹት። ከተክል እና የሰብል ልማቱ ጎን ለጎንም የማር ምርት ላይ የሠጠው ትኩረት የአካባቢ እምቅ ፀጋ የመጠቀም ዕይታ በግሉ ዘርፍ እየሠረፀ መሆኑ የታየበት ነው ብለዋል። በእርሻው የዶሮ እርባታ፣ የንብ ማነብና የእንስሳት ልማት የተጀመረ ሲሆን የመኖ ዝግጅት መጀመሩም ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ ስኬታማ የልማት ጉዞ የዜጎችን ተጠቃሚነትና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት እያረጋገጡ ነው
Apr 27, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ስኬታማ የልማት ጉዞ የዜጎችን ተጠቃሚነትና የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት እያረጋገጡ መሆኑ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ። ከትናንት ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ሥራ አፈፃጸም ግምገማ ተጠናቋል። በዚሁ ወቅት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ በመዲናዋ ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ተሞክሮ የሚሆኑ የልማት ስኬቶች ተገኝተዋል ብለዋል።   የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶችም ሕብረብሔራዊ አንድነትን በማፅናት በዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ያመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢኮኖሚ መስክም ግዙፍ ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት በመገንባት የመዲናዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያንፁ ውጤታማ የልማት ስኬቶች መገኘታቸውን አስረድተዋል። የአዲስ አባባ አስደናቂ የልማት ስኬቶች የኢትዮጵያ የብልፅግና ተምሳሌት ከተማ የመገንባት ዕሳቤን በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። የመዲናዋ ዘርፈ ብዙ የልማት ስኬቶች የመዲናዋን ነዋሪዎች የአኗኗር ሥርዓትን በማዘመን ተጠቃሚነትን እያረጋገጡ መሆኑን አንስተዋል።
የሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ የብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሙዚየምን ጎበኙ
Apr 27, 2026 90
‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19 /2018(ኢዜአ)፦ የሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ የብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሙዚየምን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ በሙዚየሙ የተደረገ ጥልቅ የታሪክ ጉዞ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የሞዛምቢክ ፕሬዝዳንት የሙዚየም ጉብኝት በኢትዮጵያ እያደረጉት ያለው ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አካል እንደሆነም ጠቁሟል። ጉብኝቱ የኢትዮጵያን ነፃና ጥንታዊ ሥልጣኔ የሚያሳይ መሆኑን የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፤ የሀገሪቱ ታሪክና ቅርሶችም ለታማኝና ባለርዕይ አጋርነቷ ህያው ምስክሮች መሆናቸውን አመልክቷል። ኢትዮጵያ ምድረ ቀደምት መሆኗን የሚያሳዩ ታሪካዊ ቅርሶቿን ስታጋራ፣ ጥንታዊ ጥንካሬዋ ለዘመናዊውና ለውጥን ለሚያረጋግጠው አጋርነቷ መሠረት መሆኑን በድጋሚ ማረጋገጧን ጽሕፈት ቤቱ ገልጿል። ጉብኝቱ አፍሪካውያን ወንድሞቻችን ለጋራ የወደፊት ዕጣ-ፈንታ በአንድነት ለመሥራት ወደ ሁለተኛ ቤታቸው እንዲመጡ ጥሪ የሚቀርብበት መሆኑንም አመልክቷል።
አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ ናቸው
Apr 27, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ላለፉት ሁለት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ዛሬ ተጠናቋል። የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብና አበባ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት በውጤታማነት መረጋገጥ ጀምረዋል። በግምገማው የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም የተታየ ሲሆን፤ በቀሪ ወራት የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት ማጠናቀቅ ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ የእቅድ አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባዋ፤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከተያዘው ዕቅድ ውስጥ በአጠቃላይ 96 በመቶ መፈጸም መቻሉን ተናግረዋል። በዚህም በሁሉም ዘርፎች አዲስ አበባን የኢትዮጵያ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን አብራርተዋል። በመዲናዋ የነዋሪውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ በተለይም በሰው ተኮር ተግባራት የዜጎችን ሕይወት ከመሠረቱ የቀየሩ በርካታ ፕሮጀክቶች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም ከመኖሪያ ቤቶች ግንባታ በተጨማሪ የምገባ ማዕከላት፣ የተማሪዎች ምገባ፣ የኮሪደር ልማትና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት ሕዝብን በማሳተፍ በተከናወኑ ተግባራት የመዲናዋን ሰላም አስተማማኝ ማድረግ መቻሉንም ነው ከንቲባዋ የገለጹት። አካባቢንና ወንዞችን ሲበክል የነበረውን የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት ለማሻሻል በተደረገው ጥረት፣ ቀደም ሲል አንድ ብቻ የነበረው የቆሻሻ ማጣሪያ ባለፉት አምስት ዓመታት ወደ 43 ማደጉን ጠቁመዋል። ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በፍጥነት የመጨረስ ባህል መዳበሩን ጠቅሰው፤ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ከተማ ከማድረግ አኳያ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆስፒታሎች መገንባታቸውንም ተናግረዋል። የአገልግሎት አሰጣጥን ከሌብነትና ከብልሹ አሠራር ለመከላከል በተከናወኑ ተግባራት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥን ማሳለጥ መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ የዋጋ ንረትን ከመከላከል አኳያም በከተማዋ የመግቢያ በሮች የገበያ ማዕከላት መገንባታቸውን ጠቅሰው፤ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች መስፋፋታቸውን ጠቁመዋል፡፡
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ትውልዱ በቴክኒክና ሙያ ያገኘውን ክህሎት ለእድገት በተግባር መተርጎም ይጠበቅበታል
Apr 27, 2026 45
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018(ኢዜአ)፦ ትውልዱ በቴክኒክና ሙያ መስክ የሚያገኛቸውን ክህሎቶች በተግባር በመተርጎም ለእድገት የበኩሉን ሚና ሊጫወት እንደሚገባ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ገለጸ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ100ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዩቤልዩ በዓል የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት "ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ ለቀጣዩ ትውልድ" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ተከብሯል። በሥነ-ሥርዓቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮሌጁ መምህራንና ተማሪዎች፣ የቀድሞ ተማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በመድረኩ በኮሌጁ የተሰሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አውደ-ርዕይ፣ የኪነ-ጥበብ ስራዎችና የባህል አልባሳት ትዕይንት ቀርበዋል። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሚደቅሳ ከበደ በዚሁ ወቅት፤ የከተማ አስተዳደሩ የገበያውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ብቁ ሙያተኛ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ሰልጣኞች በቂ ክህሎት እንዲጨብጡ ከኢንዱስትሪዎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት ከቴክኖሎጂ ዕውቀት ውጪ ልማትና ዕድገት ማረጋገጥ እንደማይታሰብ ጠቁመው፤ በዚህ በኩል ተማሪዎች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በብቃት ሊወጡ ይገባል ብለዋል። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን ተሾመ ፈይሳ በበኩላቸው፤ ባለፉት አሥርት ዓመታት እንጦጦ በሚል ስያሜ ሲጠራ የቆየው ኮሌጅ፤ ዛሬ "ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" ተብሎ በይፋ የሚሰየምበት ዕለት በመሆኑ በዓሉን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል። በዓሉን ከማክበር ባለፈ በቴክኒክና ሙያ መስክ የታነፀ ትውልድ ለማፍራት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥልበት ነው ሲሉም ተናግረዋል። የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት ደጀኔ ተዘራ እንደተናገሩት፤ ማኅበሩ ኮሌጁን ለማጠናከር በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ነው። የስያሜው መስተካከል ከ100ኛ ዓመት በዓሉ ጋር መገጣጠሙ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን በበኩላቸው፤ ኮሌጁ ለሀገር ኩራት የሆኑ በርካታ ሙያተኞችን ማፍራቱን ተናግረዋል። በቀጣይም የካበተ ልምዱን ለሌሎች የሚያጋራበት ምቹ ሁኔታ ሊመቻች እንደሚገባም ጠቁመዋል። የአልማዝ ኢዩቤልዩ በዓሉ ከመጀመሪያው ጀምሮ እስከ መዝጊያው ሥነ-ሥርዓት ድረስ ስኬታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት ምስጋና ቀርቧል።
የሰው ሰራሽ አስተውሎትን በሁሉም ተቋማት ገቢራዊ ማድረግ የሚያስችል የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት እየተገነባ ነው
Apr 27, 2026 145
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦የሰው ሰራሽ አስተውሎትን በሁሉም ተቋማት ገቢራዊ ማድረግ የሚያስችል የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት እየተገነባ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ገለጸ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ይታወቃል። ሹመቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራርና ኢትዮጵያ በአህጉሪቷ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና የተሰጠ እውቅና ነው።   የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እንደገለጸው፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት ኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን ሥነ ምግባራዊ መርሆች በተከተለ መልኩ በማልማት፣በመመራመር እንዲሁም ተግባራዊ በማድረግ በኩል ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር እንድትሆን ለተሰሩ ስራዎች እውቅና የሰጠ ነው። በኢትዮጵያ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለመክፈት የሚያስችሉ ዝግጅቶችን ጨምሮ በዘርፉ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።ለዚህ ስኬትም የተለያዩ ተቋማት በቅንጅት በርካታ ስራዎችን እያከናወኑ ይገኛሉ። በዚህም የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ሀገርን በአፍሪካ ቀዳሚ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬትና ለዲጂታል ኢትዮጵያ-2030 ዕቅድ አዳዲስ የፈጠራ ዕሳቤዎችን በማፍለቅ ጉልህና ገንቢ ሚና እየተወጣ ነው።   የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በለጠ እሱባለው ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለአመራር ልህቀትና ቴክኖሎጂ ልማት አስገዳጅ እየሆነ መጥቷል። የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርኩም የሰው ሰራሽ አስተውሎት መሠረተ ልማት በማስፋፋት በኢትዮጵያ አስቻይ የዲጂታል ከባቢ ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የፋይበር፣ ፓወርና ሌሎች የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን በማሟላት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሥርዓትን የሚያዘምን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ከግብ ለማድረስም በሰው ሰራሽ አስተውሎትና በዲጂታል ክህሎት የበለጸገ የሰው ሃይል ማፍራት እየተቻለ መሆኑን አስረድተዋል። የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ የቦርድ ሊቀ መንበርና የአፍሪካ ቴክኖሎጂ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ባህሩ ዘይኑ፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል መሠረተ ልማት ወሳኝ ሽግግር እያደረገች ነው ብለዋል።   ለአብነትም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓለም አቀፍ ተፅዕኖን በመገንዘብ ኢንስቲትዩት በማቋቋምና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ የመክፈት ዝግጅት መኖሩ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። የግሉ ዘርፍም የዲጂታል ልማት አስቻይ የፖሊሲ ማዕቀፎችን በመጠቀም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን የሚያሳልጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያን ማልማት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚም የኢትዮጵያን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕውቀትና ክህሎት ለማሳደግ እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ተባባሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር ሸጋው አናጋው፤ የተቋማትን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ትግበራ ለማፋጠን የስልጠና አቅም ወሳኝ ነው ብለዋል።   የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲም በዘርፉ በዕውቀትና ክህሎት የበለጸጉ ዜጎችን በማፍራት ሁሉንም ተቋማት ብቁ የዲጂታል መሠረተ ልማት ለማስታጠቅ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። የሁሉንም ተቋማት የዳታ ሥርዓት የማሰባሰብና መተንተን አቅም ለማጎልበት የመንግስትና የግል ተቋማት ትብብርን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በቀጣይም በኢትዮጵያ የስታርት አፕ ፖሊሲ ማዕቀፍ በዳታ ሳይንስ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎትና በሮቦቲክስ ዘርፍ ብቁ ወጣቶችን ለማፍራት የግሉን ዘርፍ አቅም ለማጠናከር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
መንግስት ለወጣት የዲጂታል ሥራ ፈጣሪዎች ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር ባለፈ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ ነው
Apr 25, 2026 390
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መንግስት ለወጣት የፊንቴክ ስታርትአፖች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር ባለፈ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢንተርፕሪነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት (EDI) እና ከተባበሩት መንግሥታት ካፒታል ልማት ፈንድ (UNCDF) ጋር በመተባበር፣ ላቅ ያለ የፈጠራ ሥራ ላሳዩ ስምንት የፊንቴክ (FinTech) ስታርትአፖች የገንዘብ ሽልማት መርሀ ግብር አካሂዷል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ መንግሥት ለወጣት የዲጂታል ሥራ ፈጣሪዎች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር ባለፈ ተገቢውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።   መርሐ ግብሩ በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍን ለማዘመንና የወጣቶችን የፈጠራ አቅም ለማበረታታት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። የፊንቴክ መፍትሔዎች ለግብርና፣ ለቱሪዝም፣ ለኢንዱስትሪና ለጠቅላላው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያላቸው ፋይዳ የላቀ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። ለዚህም በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ እንደ ቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብር ያሉ ውጤቶች ለበርካታ ዜጎች የፋይናንስ ተደራሽነትን ማሳደጋቸውን በአብነት ጠቅሰዋል።   የዘርፉን ተደራሽነት ለማስፋት ወጣቶች የሚፈጥሯቸው ዲጂታል መፍትሔዎች ለዲጂታል ሽግግር ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አስገንዝበዋል። ከ300 በላይ የፊንቴክ ስታርትአፖች መካከል 33ቱ ተለይተው ለፉክክር መቅረባቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በዛሬው ዕለት ስምንት ምርጥ ስራ ፈጣሪዎች አሸናፊ በመሆን ከአጋር ድርጅቶች የተገኘውን የ20 ሚሊዮን ብር ሽልማት አግኝተዋል ብለዋል። አሸናፊዎቹ የተሰጣቸውን የገንዘብ ድጋፍ የንግድ ሞዴሎቻቸውን በተጨባጭ የገበያ ሁኔታ ለመፈተሽና ለማሳደግ እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል።   ከተሸላሚዎቹ መካከል የአበዳሪ መተግበሪያ ፈጣሪ ፌቨን ሽመልስ እና የኡጆ መተግበሪያ ፈጣሪ አቤኔዘር እንግዳ፣ መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት አድንቀዋል። ከተሸላሚዎቹ መካከል የ"አበዳሪ" መተግበሪያ ፈጣሪ ፌቨን ሽመልስ በበኩሏ፤ የብድር አቅርቦትና አሰባሰብን የሚያቀላጥፍ ቴክኖሎጂ በማበልጸግ ለዘርፉ መፍትሄ ማቅረቧን ገልጻለች። በተመሳሳይ የ"ኡጆ" መተግበሪያ ፈጣሪ አበኔዘር እንግዳ፣ ባህላዊውን የዕቁብ ሥርዓት በቴክኖሎጂ ለማዘመን ለጀመረው ሥራ መንግሥት የሰጠውን ትኩረትና ድጋፍ አድንቋል። ሽልማቱ ለጀመሩት የፈጠራ ሥራ መነሻ ካፒታል ከመሆኑ ባለፈ፤ ለሌሎች ወጣቶችም ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትና አላስፈላጊ ወጪን አስቀርቶልናል - ተገልጋዮች
Apr 25, 2026 128
ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልት እና ያልተገባ ወጪን እንዳስቀረላቸው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ከተማ ተገልጋዮች ገለፁ፡፡ በማዕከሉ አገልግሎት በማግኘት ላይ የነበሩት አቶ ዮናስ ሴራሞ ለኢዜአ እንደገለፁት ፤የገቢ ግብር ጉዳይ ላይ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ማዕከሉ እንደመጡና ባጠረ ጊዜም የሚፈልጉትን ፈጽመው ለመመለስ መቻላቸውን ነው የሚገልጹት።   የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተገልጋይን ከአላስፈላጊ ከሆነ እንግልትና ወጪ እንደሚታደግ በተግባር ያረጋገጡ መሆኑንም ተናግረዋል። የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ለማውጣት ወደ ማዕከሉ የመጣው ወጣት ሞላልኝ ታምራት በወቅቱ አገልግሎቱን ማግኘቱን እና ማዕከሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይታይ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር በመቅረፍ ለማሕበረሰቡ አስፈላጊ የሆነ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ነው የገለጸው።   በማዕከሉ የተገልጋዩን ክብር የጠበቀ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኝቷ እንዳስደሰታት የምትገልፀው ደግሞ ወጣት በረከት ዱቲሶ ናት፡፡   በፋይዳ መታወቂያዋ ላይ ያጋጠማትን የስም ስህተት በአጭር ጊዜ ማስተካከል ችያለሁ ብላለች። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ከበደ ሻሜቦ ማዕከሉ በስምንት ተቋማት 27 አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡   እስካሁን ድረስ ከ 20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠት መቻሉንም አስረድተዋል፡፡ በከተሞች በመሬት ዘርፍ የሚሰጡና ለብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሆኑ አዳዲስ 48 አገልግሎቶች ተለይተዉ በማዕከሉ ውስጥ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻልም ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል፡፡
ስፖርት
ማንችስተር ዩናይትድ ከብሬንትፎርድ ጋር ይጫወታል
Apr 27, 2026 108
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ):- የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ በማንችስተር ዩናይትድ እና በብሬንትፎርድ መካከል ዛሬ ይደረጋል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኦልድትራፎርድ ስታዲየም ይካሄዳል። ማንችስተር ዩናይትድ በ58 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ብሬንትፎርድ በ48 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ ሲገናኙ የአሁኑ ለ10ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ ብሬንንትፎርድ በሶስቱ ድል ቀንቶታል። በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። ባለፉት አምስት የሊግ ግንኙነታቸው ሁለቱም በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ሲያሸንፉ አንድ ጊዜ አቻ ወጥተዋል። ብሬንትፎርድ ከዩናይትድ ጋር ያደረጋቸውን ያለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች አሸንፏል። በ33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቼልሲን 1 ለ 0 ያሸነፈው ማንችስተር ዩናይትድ ተከታታይ ድሉን ካስመዘገበ በሻምፒዮንስ ሊጉ የመሳተፍ እድሉ የበለጠ ሰፊ ይሆናል። ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች አቻ የወጣው ብሬንትፎርድ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ እና የአውሮፓ መድረክ ተሳትፎውን ለማረጋገጥ ይጫወታል። የ40 ዓመቱ ክሪስ ካቫናግ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ላይ ማዕከል ያደረገ ውጤታማ የልማት አቅጣጫ ላይ ናት 
Apr 27, 2026 265
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ላይ ማዕከል ያደረገ ውጤታማ የልማት አቅጣጫ ላይ ናት ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ። የአየር ንብረት ኢንቨስትመንት ፈንድስ(CIf) ከኢትዮጵያ መንግሥት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ የልምድ ልውውጥ ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በጉባኤው ላይ ምሁራን፣የልማት አጋሮችና ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ጨምሮ አምባሳደሮችና የሀገራት ተወካዮች ተገኝተዋል።   ለሶስት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ ላይ የተለያዩ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ያገኟቸው ውጤቶች ላይ ተሞክሮዎችን አቅርበው የልምድ ልውውጥ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የዕድገት ራዕይና አቅጣጫ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ላይ ማዕከል ያደረገ ነው። ለዚህም ታዳሽ ሃይልን ማስፋፋት፣የውሃ አቅርቦት ማሻሻል፣ የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ በማድረግ የማህበረሰቡን የመቋቋም አቅም የሚያሳድጉ ውጤታማ ተግባራት መከናወኑን አብራርተዋል። የአዲስ አበባ የኮርደር ልማትና የወንዝ ዳር ልማት ስራዎች ከተማዋን ዘመናዊ ከማድረጋቸውም ባሻገር እድገት ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በተናበበ መልኩ እንዴት እንደሚከወን ማሳያ ነው ብለዋል። መንግሥትም ከአየር ንብረት ለውጥ ኢንቨስትመንት ፈንድስ ጋር በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ በአማራጭ ሃይል አቅርቦቶች እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረጉ መፍትሔዎች ላይ ውጤታማ ተግባራት ማከናወኑንም አመልክተዋል። የዛሬው የልምድ ልውውጥ ጉባኤ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ዙሪያ ያላትን ተሞክሮ ለማካፈል፤ ከሌሎች ተሳታፊዎችም ለመማር ዝግጁ ናት ሲሉም ገልጸዋል። የአየር ንብረት ኢንቨስትመንት ፈንድስ(CIF) ዋና ስራ አስፈጻሚ ታሪዬ ባድጌሲን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል በአረንጓዴ አሻራ አርዓያ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ከዚህ ቀደም ስኬታማ በሆነ መንገድ ማስተናገዷም በዘርፉ ያላትን የላቀ ተሞክሮ ያሳያል ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድስ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በጋራ የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በአማራ ክልል ከ22 ሚሊዮን በላይ የቡናና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል
Apr 27, 2026 186
ባህርዳር፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በመጪው ክረምት ለሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ22 ሚሊዮን በላይ የቡናና የሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች መዘጋጀታቸው ተገለጸ። ‎በቢሮው የሆርቲካልቸር ባለሙያ አቶ አወቀ ዘላለም ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በክልሉ ተስማሚ ስነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በመለየት ቡናና ሌሎች ፍራፍሬዎችን በክላስተር የማልማት ስራ እየተካሄደ ነው። ‎በተያዘው በጋ ወቅትም ከፍተኛ ምርት የሚሰጡና በሽታን የሚቋቋሙ ከ22 ነጥብ አራት ሚሊዮን በላይ የቡናና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።   ‎ለተከላ ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል ወደ 12 ነጥብ 2 ሚሊዮን የሚጠጋው የቡና ችግኝ ሲሆን ቀሪው ደግሞ የቆላና የደጋ ፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን ተናግረዋል። ‎‎ክልሉን በቡናና ፍራፍሬ ልማት ሞዴል ለማድረግም ሽፋኑንና ምርታማነቱን በማሳደግ ላይ በማተኮር የአርሶ አደሩ ዘላቂ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ‎‎‎ለመጪው ክረምት ለተከላ እየተዘጋጀ ያለው ችግኝም ከ32 ሺህ ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ የሚተከል መሆኑን አስረድተዋል። ‎‎በምዕራብ ጎጃም ዞን የጃቢ ጠህናን ወረዳ አርሶ አደር ተፈራ መለሰ ፤ ባለፉት ዓመታት በአንድ ሄክታር መሬት ላይ ቡናን የማልማት ስራ መስራታቸውን ጠቅሰዋል።   በመጪው የክረምት ወቅትም በተጨማሪ ሩብ ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝን በኩታ ገጠም ለመትከል አቅደው እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል። ‎‎የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በመትከል የተሻለ ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን የገለፁት ደግሞ የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ውበት ተስፌ ናቸው። ‎ባለፈው ዓመት የክረምት ወቅት ከተተከሉ ወደ 17 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚጠጋ ቁጥር ያላቸው የቡና፣ የቆላና ደጋ ፍራፍሬ ችግኞች 93 ነጥብ 5 በመቶው መጽደቁን የቢሮው መረጃ ያመለክታል፡፡
ለአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚና ላቀ ነው
Apr 24, 2026 129
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ለምግብ ዋስትና መሰረት ለሆነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የላቀ ሚናቸውን ማስቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡ የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ከክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ጋር በመተባበር በአረንጓዴ አሻራ ልማት ዙሪያ ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በሆሳዕና ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡   በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር እንደገለጹት፤ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ ትግበራ ከደን ልማቱ ባለፈ የስነ ምግብ ዋስትና መሰረት እየሆነ መጥቷል። በልማቱ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ያላቸውንና ለምግብ የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎችን በብዛትና በስፋት የማልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ለተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ለምግብ ዋስትና መሰረት ለሆነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አንስተዋል። የስልጠናው ዓላማም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በእውቀትና መረጃ ላይ የተመሰረተ መረጃ ለህዝብ ተደራሽ ማድረግ እንዲችሉ መሆኑን ገልጸዋል።   የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ዘሪሁን እሸቱ፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን በሚገባ ተገንዝበው የተሟላ መረጃ ለህዝብ ተደራሽ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። ለዚህም መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ወሳኝ እንደሆኑ አንስተው በቀጣይም በሙያቸው የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ በማስቀጠል ልማቱን እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት፤ የኮሙኒኬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ ይኖራቸዋል
Apr 24, 2026 127
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረውን የአየር ሁኔታ ትንበያ አስመልክቶ ለኢዜአ መግለጫ ልኳል፡፡ በዚህም በሚቀጥሉት አስር ቀናት በርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚያገኙ አመላክቷል፡፡ በመግለጫው በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል፣ የስምጥ ሸለቆና አጎራባች አካባቢዎች፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እንዲሁም ሰሜን ምዕራብ እና ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚኖራቸው አስታውቋል፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች የሚኖረው ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ለቋሚ ተክሎች ዕድገት፣ ለግጦሽ ሳርና ለውሃ አቅርቦት መሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጿል። በሌላ በኩል ከዝናቡ ጋር ተያይዞ የመሬት መንሸራተት፣ የአፈር መሸርሸር እና ድንገተኛ ጎርፍ አደጋዎች ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብሏል፡፡ በተጨማሪም በተደፋታማ ማሳዎች ላይ ውሃ መተኛት፣ የሰብል በሽታና ተባይ መከሰት እንዲሁም የአረም መስፋፋት ሊከሰት እንደሚችል ጠቅሷል፡፡ በዚህም በከተሞች በቆሻሻ የተደፈኑ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦዎችን ማጽዳትና የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎችን መሥራት ይገባል ብሏል በመግለጫው፡፡ የአፈርና ውሃ እቀባ ስራዎች እንዲሁም የእርከን ስራዎችን ማጠናከር፣ የሰብል በሽታና አረምን አስቀድሞ መከላከል እንዲሁም የእንስሳት መኖ መሰብሰብ እንደሚገባም አመላክቷል፡፡ በተጨማሪም ዝቅተኛ እርጥበት በሚገኝባቸው አካባቢዎች የዝናብ ውሃን በማሰባሰብና ደጋፊ መስኖን በመጠቀም የትነት መጠን የሚያስከትለውን ጉድለት መሙላት እንደሚገባ አስታውቋል፡፡ በአባይ፣ ባሮ አኮቦ፣ የላይኛው ኦሞ ጊቤ፣ ገናሌ ዳዋ እና ስምጥ ሸለቆ ተፋሰሶች ላይ ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ የገፀ-ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖርም በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ይህም ለኃይል ማመንጫ፣ ለመስኖና ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሻሻል ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁሞ፤ ህብረተሰቡ የጎርፍ አደጋን ለመከላከልና የሚገኘውን እርጥበት በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባውም አሳስቧል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸውን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ አለባቸው
Apr 27, 2026 103
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦‎ አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸው ላይ እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከታንዛኒያ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የአፍሪካ ወሳኝ ማዕድናትን ለአረንጓዴ የኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ማዋል" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጁት የ12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ቅድመ ጉባኤ ተካሂዷል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ እንደ ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ግራናይት እና ሌሎች የከርሰ ምድር ሀብቶችን ጨምሮ የዓለምን 30 በመቶ ማዕድናትን ይዛለች፡፡ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻዋን የዓለምን ከፍተኛ የኮባልት ማዕድን የያዘች መሆኑን ገልጸው፤ ይሄውም አፍሪካን የዓለም አቀፍ የኃይል ሽግግር /Energy Transition/ ማዕከል ያደርጋታል ብለዋል፡፡ አፍሪካ ዩራኒዬምና ሌሎች የከርሰ ምድር የከበሩ ማዕድናት ባለቤት መሆኗን በመጥቀስ፤ ለዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል አቅርቦት አስተዋጽኦ ከማድረግ ባለፈ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ኒውክሌር ኃይል ልማት እያመሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አፍሪካ የከበሩ ማዕድናት ባለቤት ብትሆንም አብዛኛው በጥሬ እቃ መልክ ወደ ውጭ የሚላክ በመሆኑ የአህጉሪቱ የእርስ በእርስ ግብይት ከሁለት በመቶ እንዳማይዘል ተናግረዋል፡፡ በአህጉሪቱ የማዕድናት ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን መገንባት ቢቻል በየዓመቱ ከ24 ቢሊየን ዶላር በላይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘትና ለ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ይቻላል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ የማዕድን ፖሊሲ ለእሴት መጨመር፣ ኢንዱስትሪ ልማትና ሁሉን አቀፍ ልማት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአህጉሪቱ የተቀናጀ ቀጣናዊ ኢንዱስትሪ ለመገንባት ያለውን ፍላጎት በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አህጉራዊ የማዕድን ሀብቶችን ወደ ዘላቂ ብልጽግና መለወጥ ይገባል ብለዋል፡፡ በዚህም የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቀጣናዊ እሴት ሰንሰለትን በማጠናከር የማዕድን ጸጋዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚደረገው ጥረት ትብብሩን ማጠናከሩን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካዳሪ ሲንጎ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍና አካታች ዕድገት ለማስመዝገብ የማዕድን ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በተፈጥሮ ሀብታችን ላይ የሚኖረን ትብብርና ተሳትፎ ስትራቴጂያዊና መዳረሻ ግብ ያለው መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮት ሽግግርን ለመፈጠር በአቅም ግንባታ ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 510
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 407
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 692
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት።   ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።   የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 26, 2026 100
ክልሎች፤ሚያዝያ 18 /2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር የምንቃኝበት ነው። በዚህ ሳምንትም አንኳር የክልሎች ክንውኑን የሚያሳዩ መረጃዎች ቀርበዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተም! ኢትዮጵያ የበጋ መስኖ ልማት ስራ መደባኛ ስራዋ ካደረገች ወዲህ አያሌ ለውጦች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ባለፉት ዓመታት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በእቅድ እና በቁርጠኝነት በመከናወኑ ከውጪ የሚገባ ስንዴ ቀርቷል፤ የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጥረቱም ቀጥሏል። ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚደረገው ሽግግርም ዓመቱን ሙሉ በማልማት እየታጀበ ሲሆን የአንበሳውን ድርሻ የሚይዘው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሥራ ነው። በዚህ ውስጥ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አበረታች ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በተያዘው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ወሬርሶ ማሊማ፣ በጂዳ ወረዳ ሲባ ሲርቲ እና ቂምቢቢት ወረዳ ሰገሌና ደርማሙሳ ቀበሌ በኩታ ገጠም የለማ እና በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ የስንዴ ቡቃያ አስቃኝተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፎቶ ጋር ያያዙት መልዕክትም ''ይህ የበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት በምግብ ራስን የመቻል እና የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተማችን ነው'' ይላል። ብሪክስ -- ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በባህር ዳር ከተማ ''የብሪክስ አሁናዊ አቅሞች እና የኢትዮጵያ የልማት ትብብር ትኩረቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ጉባኤ አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ በመሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑ ይታወቃል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሐመድራፊዕ አባራያ በመድረኩ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ሳትፎዋን በማሳደግ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የተደራጁ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። መድረኩም ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችላት የሁለትዮሽ ትብብር ጭምር የተካሄደበት፤ በብሪክስ ማዕቀፋ በተለይም በግብርና እና ስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና መሰል ዘርፎች ልምድ የተሰጠበትም መሆኑ ተመላክቷል። ማረም እና ማነጽ የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል እንዲሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት መሰጠቱ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነው። የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነሮች የጋራ ጉባኤ “የማረሚያ ተቋማት ለሀገር ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል ሆነው እንዲያገለግሉ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከታራሚዎች የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የመሰረታዊ ፍላጎት አቅርቦት፣ ከማረሚያ ቤት የሪፎርም ሥራዎች እንዲሁም ከማረም የማነጽ ተሃድሶ ልማት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ጉባኤው በልዩ ሁኔታ የመከረበት ነው። ኢትዮጵያ ማምረቷን ቀጥላለች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የራስን አቅም የመገንባት ታሪካዊ ጉዞ እንደቀጠለ ነው። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል "ድሬ ታምርት ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ በተዘጋጀ የአምራች ኢንዱስትሪ ኤክሲፖ ላይ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ በተደረገው ድጋፍና ክትትል እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በንቅናቄው የተዘጉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲመለሱ በማድረግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በጥራትና በስፋት እየተተኩ ነው ብለዋል። ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድም መሠረታዊ ውጤቶች ተገኝተዋል ነው ያሉት። ዘንድሮ ብቻ 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ የውጭ ሀገራት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት መዘጋጀታቸውም ተገልጿል። ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል በኢትዮጵያ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ውኃ የህልውና ጉዳይ ነው። በእርግጥ ለፍጡራን ሁሉ ውኃ ህይወት ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ግን ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል። በሳምነቱም በአፋር ክልል ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የአይሳኢታ አፋምቦ የብዙሃን መንደር እና የአይሳኢታ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተከናወነው ልማት የህብረተሰቡን ጥያቄዎች በተግባር ከመመለሱ በላይ፣ በየደረጃው ያለውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፤ መንግስት የውሃ ሽፋን አነስተኛ ለሆነባቸው አካባቢዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት፣ በፕሮጀክቶች ታግዞ መስራት እንደሚገባ በጽኑ ያምናል፤ በተለይም የለውጡ መንግስት ለቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች በሰራው ስራ የውኃ ተደራሽነት በእጅጉ ማደጉን አንስተዋል። ልምድ ልውውጥ እና ተሞክሮ -ለምክር ቤቶች ሌላው ቅኝታችን በዚህ በተጠናቀቀው ሳምንት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤትና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ መካሄዱን የዳሰሰ ነው። የጋራ የምክክር መድረኩ ዓለማ የልምድ ልውውጥና የልማት ሥራዎችን በመመልከት ተሞክሮ መለዋወጫ ነው።የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ፤ መንግስት ሕዝቡ የሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የምክር ቤቶችን አደረጃጀት ማጠናከርና የክልሉ ሕገ መንግስት ያስቀመጣቸውን ኃላፊነቶች መፈጸም ይገባል ብለዋል።የመንግስት የልማት ኢኒሼቲቮች የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል የሚያስችሉ በመሆናቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መተግበር እንዲችሉ ምክር ቤቶች ያለሰለሰ ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተመልክቷል። የጤና ልማት ስራ እስከ አክሞ ማዳን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ በሚደረግ ጥረት የአጋር ድርጅቶች አስተዋጾ ትልቅ ድርሻ እንዳለውም የተመለከተው በዚህ ሳምንት ነው። ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጋር በመሆን በአርባ ምንጭ ከተማ ያስገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ መሰል የጤና ዘርፍ የልማት ስራዎች መንግስት በዘርፉ የያዘውን ውጥን ከማሳካት አንጻር እገዛቸው ትልቅ መሆኑን አንስተዋል።ማዕከሉ ማህበረሰቡ በቅርበት ሕክምና እንዲያገኝ ከማስቻል ባለፈ ወደ ሌላ አካባቢ ሄዶ ሲታከም ሊያወጣ የሚችለውን ወጪ ያስቀራል። ማዕከሉ የኩላሊት እጥበት ማሽኖች፣ የመድሃኒት ቤት፣ መኝታ አልጋዎችና የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሟልቶ የተገነባ መሆኑም ታውቋል። የከተሞች ኮሪደር- ከቱሪዝም እስክ ኮንፍረንስ ማዕከልነት በኮሪደር ልማት እጅግ ከተዋቡ እና ከደመቁ የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል ሀዋሳ አንዷ ናት። በሳምንቱ የከተማዋ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ማጠናቀቂያ የምስጋናና ዕውቅና እንዲሁም የአራተኛ ዙር የኮሪደር ልማትና የሐይቅ ዳርቻ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄዷል፡፡ የሲዳማ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርቡ ቀጥሏል ብለዋል። በቀጣይ ለሚከናወነው የኮሪደር እና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ስራዎች እንደሚቀጥሉ አንስተው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጎላ መሆኑን ገልፀዋል። የከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነት ለማጠናከር ሥራዎች በላቀ ፍጥነትና ጥራት መከናወናቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ምርጫ -የዴሞክራሲ መሰረት ሳምንቱ በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ከመጠናቀቁ በፊት መራጮች የምርጫ ካርድ ወስደው ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹበትም ነበር። ኢትዮጵያዊያን መጪውን ጊዜ የተሻለ የሚያደርግላቸውን መንግስት ለመመረጥ ዝግጅታቸውን በተግባር እያረጋገጡ ነው።
ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር
Apr 23, 2026 247
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ መጀመሯን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል። ጋዜጠኛ ዳንኤል ኦሊቫሬስ ጋሌጎ በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ እንደገለጸው፣ ይህ ሜጋ ፕሮጀክት አፍሪካውያን ተጓዦች ከአህጉሩ ውጭ ባሉ እንደ ዱባይ፣ ፓሪስና ለንደን ባሉ ማዕከላት በኩል የሚያደርጉትን አድካሚ ጉዞ በማስቀረት፣ አዲስ አበባን የአህጉሪቱ ቀዳሚ የመገናኛ ማዕከል ለማድረግ ያለመ ነው። ከአዲስ አበባ ከተማ በስተደቡብ ምስራቅ 48 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ግንባታ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ተብሎ መጠቀሱን ጋዜጠኛው በዚሁ ጽሁፉ አመልክቷል።   ስራው በይፋ የተጀመረው ባለፈው ጥር ወር ሲሆን፣ አውሮፕላን ማረፊያው በ2023 ዓ.ም (2030 እ.ኤ.አ) የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር፣ በዓመት 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም እንደሚኖረው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ተመልክቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ፣ ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። ይህም አውሮፕላን ማረፊያውን በዓለም ላይ በርካታ ተጓዦችን ከሚያስተናግደው የአትላንታው ሀርትስፊልድ-ጃክሰን አውሮፕላን ማረፊያ ካለው አቅም በላይ እንደሚያደርገው ዳንኤል ኦሊቫሬስ ጋሌጎ ባሰፈረው ጽሁፍ አብራርቷል። አውሮፕላን ማረፊያው ከመንገደኞች አገልግሎት ባለፈ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠናን (AfCFTA) በላቀ ሁኔታ ለመደገፍ ታቅዶ የተገነባ መሆኑን ጋዜጠኛው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ በዝርዝር አስቀምጧል።   በዓመት 3 ነጥብ 73 ሚሊዮን ቶን ጭነት የማስተናገድ አቅም ያለው ይህ መሠረተ ልማት፣ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የአፍሪካን የጭነት በረራ ፍላጎት በሚገባ ምላሽ መስጠት የሚችል መሆኑን ተጠቁሟል። የአውሮፕላን ማረፊያው የተርሚናል ዲዛይን በዓለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ በሆነው ዛሃ ሃዲድ አርክቴክትስ የቀረበ መሆኑን የጠቀሰው ጋዜጠኛው፣ዲዛይኑ የኢትዮጵያን ታላቁ ስምጥ ሸለቆና የተለያየ መልክዓ ምድራዊ ውበትን የሚያንፀባርቅ መሆኑን በጽሁፉ አካቷል። ተጓዦች በአውሮፕላን ማረፊያው ውስጥ ሲዘዋወሩ የኢትዮጵያን ባህልና ተፈጥሮ እንዲመለከቱ በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፣ለዘላቂነት ቅድሚያ በመስጠት የፀሐይ ብርሃን ኃይልንና የዝናብ ውሃ አሰባሰብ ስርዓትን እንዲጠቀም ተደርጎ ተቀርጿል።   በአጠቃላይ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጠናቀቅ፣ኢትዮጵያ በአፍሪካ አቪዬሽን ያላትን መሪነት ከማረጋገጡ ባለፈ የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ትስስር ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ጋዜጠኛው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ደምድሟል። ይህ ፕሮጀክት ከሌሎች የአፍሪካ አየር መንገዶች ጋር በመተባበር የነጠላ የአፍሪካ አየር ትራንስፖርት ገበያን (SAATM) ወደ ተግባር ለመቀየር የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እንደሚያግዝም ተመልክቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 19, 2026 344
የምግብ ሉዓላዊነት - ከተረጂነት መላቀቂያው መንገድ በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ ከተረጂነትና ጠባቂነት መፋቻ መንገዶች መካከል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አንዱ ብልኀት አድርጋ እየታተረች ነው። ይህን ተከትሎም የዜጎችን የምግብ ፍላጎት በራስ የምርት ዐቅም የመሸፈን ሥራ በመከወን ከጠባቂነት ለመላቀቅ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ስኬታማ ናቸው። ለዚህም ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ከልመና ወጥታ ወደ ውጭ ገበያ መላክ መጀመሯ አሥረጅ ነው። በመሆኑም ከውጭ የኢኮኖሚ ጥገኝነት በመላቀቅ የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት ለማስከበር በስንዴ ልማት የተመዘገበውን ስኬት በሌሎች የግብርና ዘርፎች ለመድገም ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም መሠረት በሩዝ፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ሻይ ቅጠል እና ሌሎች የተለያዩ ሰብሎች ላይ እየተከናወነ ያለው ሥራ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው። የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የግብርና ድርጅት (ፋኦ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምግብ ዋስትናና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ የአመራር ቁርጠኝነት የአግሪኮላ ሜዳሊያ በ2016 ዓ.ም ማበርከቱ ለምግብ ሉዓላዊነት ጥረት የተሰጠ ዕውቅና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ረሃብን ከማስቀረት ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ብሔራዊ ብልጽግናን ዕውን ለማድረግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሃብቶች፣ተስማሚ የዓየር ንብረት፣ ለሥራ ትጉ የሆነ ወጣት እንዳላት እና እነዚህን ሃብቶች ታሳቢ በማድረግ የታሪክ ዐውራ የሆነችውን ሀገር ልማት ወደፊት ለማራመድ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ እንደከፈልን ሁሉ፤ ከምግብ ጥገኝነት ለመላቀቅ በትጋት መሥራት ይገባል ሲሉ ማስገንዘባቸው ይታወሳል። የምግብ ሉዓላዊነት፣የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት፣ የበጀት ሉዓላዊነት ታላቁን የሀገር ሉዓላዊነት በጽናት የሚያቆሙ መሆናቸውንም አብራርተዋል። እነዚህን የሉዓላዊነት ዘርፎች ለማስከበርም ብሔራዊ ዐርበኝነት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። ሀገራዊ ትልሙ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት የሚያሸጋግር መልካም ጅማሮ ነው።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 19, 2026 182
ክልሎች፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የንፋስ ሃይል በቀጥታ የምናመራው በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ ነው። በኢተያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው የመረቁትን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን እንመለከታለን። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 100 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል ልማት ወደ ፊት እየተራመደች መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ሥራ ነው። ኢትዮጵያ ዘንድሮ ከጉባ እስከ አሰላ፣ ገናሌ እና አይሻ በሃይል ልማት ዘርፍ ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ፕሮጀክቶች አስመርቃለች። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ደግሞ በዚህ ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀምሯል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩም በምርቃቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ከለውጡ በፊት የነበረው 4 ሺህ ሜጋ ዋት የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በመድረስ ከእጥፍ በላይ እድገት የተመዘገበበትን ትልቅ ስኬት አንስተዋል። የስንዴና ገብስ ሰብሎችን በከፍተኛ መጠን የሚያመርተው አርሲና አካባቢው አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ሃይል የሚመረትበት አካባቢ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እናስቀጥላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። ቢሾፍቱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማም በዚህ ሳምንት በቢሾፍቱ ሀርሰዴ አዳራሽ መካሄዱ ይታወቃል። በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ስኬታማ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይም የክልሉን ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ የከተማ እና የገጠር የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ነው ያስረዱት።   ከዚህ ባለፈ የክልሉን የልማት ሥራዎች ለማቀላጠፍ የሚያግዙ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የአገልግሎት አሰጣጥ አሰራሮች መተግበራቸውንም ተናግረዋል። የቢሾፍቱ መድረክ በድምሩ የግብርና፣ የገጠርና የከተሞች ልማት፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ክንውን በዝርዝር የታየበት ውጤታማ መድረክ እንደነበረም ተመላክቷል። የአሎማ ክላስተር ሌላ የሳምንቱ ዓበይት ጉዳይ ወደ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ይወስደናል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በይፋ አገልግሎት መስጠት የጀመረው በዚህ ሳምንት ነው። በመስኖ የለማ የስንዴ ክላስተር የተጎበኘበትና በተሁለደሬ ወረዳ በክላስተር ለሚከናወነው የተቀናጀ የፍራፍሬ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ የተጀመረበት እንዲሁም የክልሉ የ10 ዓመት የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገበትን ሁነት እናገኛለን።   በእነዚህ ሁነቶች ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የመደመር መንግሥት በሁሉም ዘርፎች ለሀገር እድገትና ማንሰራራት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም በግብርና፣ በመስኖ ልማት፣ በቱሪዝምና ሌሎች መስኮች በተግባር የተመለከትናቸው የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። የአሎማ ክላስተር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የሓይቅ ዳር አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የማቻል ጥረት በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን የሚያሳዩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሀገርን የማሻገር ሥራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የታሪክ መሰነጃ የሳምንቱ በረራችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ የሰው ልጅ መገኛ፣ የኤርታሌ ትኩሳት የሚገነፍልባትና የአዋሽ ወንዝ የተንጣለለባት አፋር ክልል ገብተናል። በአፋር ቆይታችን ትኩረታችንን ሰመራ በማድረግ በስፍራው ሊገነባ የታሰበውን የሉሲ ሙዚየም እንመለከታለን። ሙዚየሙን ለመገንባት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እና የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ የፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት አድርገዋል። ለሉሲ አፋር ቤቷ ነው፤ ሀዳር የተባለው ስፍራ ደግሞ መገኛዋ ነው። በመሆኑም በዚህ ከሰው ልጅ መገኛ ጋር የተቆራኘን ስፍራ ሙዚየም ገንብቶ፣ የቱሪስት መስህብ አልምቶና አካባቢውን በስፋት አስተዋውቆ የገቢ ምንጭ ማድረግ ሲቻል ለምን ተዘንግቶ ቆየ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ይሆናል። የጊዜ ጉዳይ ሆኖ አሁን አፋር ሰመራ ላይ በሉሲ የተሰየመ የሀገር ታሪክና ቅርስ ማጣቀሻ፤ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ማሳያ የሆነ ሙዚየም ለመገንባት ዝግጅት መደረጉ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል።   የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር)፤ የሚገነባው ሙዚየም የሀገር ታሪክና ቅርስ የሚሰነድበት፣ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ተጠብቀው የሚዘልቁበት፣ የሰው ልጅ አመጣጥና ዝግመተ ለውጥ የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ የሚካሄድበት ይሆናል ብለዋል። እሳቸው እንዳሉት የሙዚየሙ ግንባታ በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገለግሎት የሚበቃ ይሆናል። የአፋር ክልል በመስኖ ቢያለሙበት፣ የጥጥ እና የቴምር ልማት ቢካሄድበት ተዝቆ የማያልቅ እምቅ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በለውጡ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን እምቅ የቱሪዝም ሃብቱንም በማልማትና በመጠበቅ የሃገር ሃብት የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የሉሲ ሙዚየም ግንባታ ሁነኛ ማሳያ ነው። የሳምንቱ ቅኝታችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ በቀጥታ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝተናል። አሶሳ በሳምንቱ በሃይማኖት አባቶች ጸሎትና ዱአ ተባርካ ስለ ሰላምና አብሮነት የሚመከርባት ከተማ ሆና እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። የተለያዩ የኃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት 7ኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ "ሰላምን ይበልጥ ለማስፋት እና ለማስረጽ የሃይማኖቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ አባቶች ስለ ሰላም እና አብሮነት እንትጋ ለትውልድ ግንባታም መስራት ግድ ይለናል በማለት አፅንኦት በመስጠት መክረዋል።   የኢትዮጵያ ሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኃይማኖቶች ለሰላም እና ለህዝቦች አብሮነት ያላቸውን አስተምህሮ በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ እና ሀገራዊ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን አለባቸው ብለዋል። በኢትዮጵያ ሰላምን ለማጽናት እና የወንድማማችነት ድልድይን ለመገንባት እንስራ በማለትም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ስንጓዝ የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ-AGRA) ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የኤልቶ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ዩኒየን የሥራ እንቅስቃሴን መጎብኘታቸውን እናገኛለን። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጥምረቱ የቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ አርሶ አደሮች ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ጥሩ ተስፋ የተሰነቀበት መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። የግብርና ልማትን የማዘመን፣ ምርታማነትን የማሳደግና የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል።   የጥምረቱ ፕሬዚዳንት አሊስ ሩህዌዛ፤ በአፍሪካ የግብርና ስርዓት ሽግግርን ለማጠናከር በተለይም አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። በአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ሂደት ውስጥ ደግሞ የኢትዮጵያ ለውጥ አስደናቂ ስለመሆኑ አንስተዋል። ሌሎች በዚህ ሳምንት በሁሉም ክልሎች ባደረግነው ምልክታ በተለይም የምርጫ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኖ ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን እየወሰዱ ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎችም የምረጡኝ ቅስቃሳ ማድርጋቸውን ቀጥለዋል። የግብርና ልማት ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እና ሌሎችም የልማት ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ የቀጠሉበት ሳምንት ነበር ማለት ይቻላል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 182
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። ‎አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። ‎በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ‎የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (‎5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (‎ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ‎‎ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። ‎‎የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ጤና ከሀገር በቀል ስኬት ወደ አህጉራዊ መሪነት
Apr 23, 2026 218
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ እያከናወነች ያለችው ስራ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂካዊ የሆኑ ተቋማዊና የፖሊሲ መሰረቶች ተጥለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መቋቋም ለሀገራዊ ችግሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ መፍትሄ ለማግኘት ትልቅ አቅም የፈጠረ ሲሆን፣ ብሄራዊ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ ተቀርጾ መጽደቁ ደግሞ የዘርፉን ልማትና አጠቃቀም በተደራጀ መንገድ ለመምራት አስችሏል። እነዚህ እርምጃዎች ሀገሪቱ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እና 2030 ስትራቴጂ ውስጥ ቴክኖሎጂውን እንደ ቁልፍ የለውጥ አቅጣጫ እንድትጠቀም በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ዘላቂ ለማድረግም በሰው ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በኮዲንግ፣ በዳታ ሳይንስ እና በክህሎት ለማሰልጠን የተጀመረው ግዙፍ ፕሮግራም የለውጡ አንቀሳቃሽ ኃይል እየሆነ ነው። ከዚህም ባለፈ፣ በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ እንዲገነባ መታቀዱና በዚህ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባልነት ውስጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት እንዲሳተፍ መወሰኑ፣ ሀገሪቱ ቴክኖሎጂውን ለውሳኔ ጥራትና ለምርምር በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀመችበት መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ እንደገለጸው፣ ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በሹመት ደብዳቤው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ AI ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አክሎ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የAI አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል እና በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ለሀገራዊ ለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ በዝርዝር አስፍሯል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የAI ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የተያዘው ሥራ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክርም ተገልጿል። ይህ አህጉራዊ እውቅና በተለይ በጤናው ዘርፍ የታዩ ውጤቶችን ያካትታል። ኢትዮጵያ በኤአይ የታገዘ ዲጂታል ኤክስሬይን ለሳንባ ነቀርሳ ምርመራ ካዋሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። በተጨማሪም የ"HEP Assist" መተግበሪያን በሙከራ ደረጃ በማስጀመር፣ በገጠር የሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ውስብስብ ምልክቶችን ሲያዩ ሙያዊ የሕክምና ውሳኔ እንዲሰጡ ድጋፍ እየተደረገ ነው። እነዚህ የዲጂታል ጤና ስራዎች በ7 ክልሎችና በ15 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ መጀመራቸው፣ ቴክኖሎጂው በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የአገልግሎት ልዩነት ለማጥበብ ያለውን ፋይዳ ያሳያል።   በአጠቃላይ፣ የኤአይ ቴክኖሎጂ በጤናው ዘርፍ ከሚሰጠው የጡት ካንሰር፣ የአንጎል እብጠትና የቆዳ በሽታዎች ምርመራ ባለፈ፣ በግብርና፣ በፋይናንስና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥም በስፋት እየገባ ይገኛል። በ2030 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ሆስፒታሎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል አገልግሎት ለመቀየር የተቀመጠው ግብ፣ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የጀመረችውን የቴክኖሎጂ ነጻነትና የመሪነት ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓት በጤና፣ በግብርና እና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በጤናው ዘርፍ እንደ ካንሰር እና ሳንባ ነቀርሳ ያሉ በሽታዎችን ቀድሞ በመለየት የህክምና ጥራትን ሲያሻሽል፣ በግብርናው ደግሞ የሰብል ተባዮችንና የቡና በሽታዎችን በመለየት ምርታማነትን እያሳደገ ነው። ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂው በመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ እና በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ሰፊ የመረጃ ትንታኔዎችን በፍጥነት በማከናወን፣ የሥራ ፍጥነትን እና የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል። የዘርፉ ፋይዳ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባለፈ የሀገሪቱን የዲጂታል ሉዓላዊነት እና የሰው ኃይል አቅም በመገንባት ላይ ያተኩራል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶችን በኮዲንግ እና በዳታ ሳይንስ በማሰልጠን እንዲሁም የፈጠራ ማዕከላትን (Startups) በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በሌሎች ላይ ጥገኛ ከመሆን ወጥታ የራሷን የዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ይህም በአህጉር ደረጃ ለሚደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች እንደ አርአያ በመሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ ፍትሃዊነት የመጠቀም ጥቅል ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አድርጎታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሹመት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ ያጎላል። በተጨማሪም ሹመቱ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና አፍሪካ በኃላፊነትና በፍትሐዊነት በታጀበ የኤአይ አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንድትሆን የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣም ያደርጋታል።
ኢትዮጵያ በአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ መንገድ
Apr 21, 2026 1457
(በዮሐንስ ደርበው) ታሪክ እንደሚነግረን፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ዕውቅና ያገኘው የኢንዱስትሪያዊ ንብረት ጥበቃን በሚመለከተው በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1883 በተፈረመው የፓሪስ ስምምነት እንዲሁም፤ በ1886 የተፈረመውን የሥነ-ጽሑፍና ሥነ-ጥበብ ሥራዎች ጥበቃን የተመለከተውን የበርን(ስዊዘርላንድ) ስምምነት ተከትሎ ነው። እነዚህ ስምምነቶችም በዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት የሚተዳደሩ መሆናቸው ይታወቃል። ኢትዮጵያ የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣንን፤ በ2022 ዓ.ም ፈጠራንና ኢኖቬሽንን በማበረታታት የፈጠራ ሐሳቦችን ወደ ዕሴት በመለወጥ ሂደት ለሀገራዊ ብልጽግና ቁልፍ ሚና የሚጫወት በአፍሪካ ተምሳሌት የአዕምሯዊ ንብረት ተቋም ለማድረግ እየታተረች ነው። ለዚህ ርዕይ መሳካትም፤ ተቋሙ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት ለሀገራዊ ፈጠራ መጎልበት፣ የኢኖቬሽን፣ ቴክኖሊጂ ሽግግር እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ማደግ ጥቅም ላይ የሚውልበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ሀገራዊ የመዋቅር ሽግግርን መደገፍ የሚል ተልዕኮ አንግቦ እየሠራ ይገኛል። የእስካሁኑ የንግድ ምልክት፣ ቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና የፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) ምዝገባ   የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ወርቅነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ2015 ዓ.ም እስከ ያዝነው በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ድረስ በንግድ ምልክት፣ በቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና በፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) 20 ሺህ 476 ምዝገባዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ 14 ሺህ 729 የንግድ ምልክቶች፣ 5 ሺህ 254 የቅጅና ተዛማጅ መብቶች እንዲሁም 1 ሺህ 781 የፈጠራ ሥራ ባለቤትነት ምዝገባ በተቋማችን አማካኝነት ተከናውኗል። የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች ምንድን ናቸው? አዕምሯዊ ንብረት ማለት በሰው ልጅ አዕምሮ የሚፈጠሩ የፈጠራ ሥራዎችን የሚመለከት መሆኑን የገለፁት አቶ ብሩክ፤ እነዚህ የፈጠራ ሥራዎች እንደማንኛውም ቁሳዊ ሀብት በንብረትነት የሚታወቁበትን አግባብ የያዘው ሥርዓት ደግሞ የአዕምሯዊ ንብረት መብት እንደሚሰኝ ያስረዳሉ። በዚህ አግባብ፤ የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች እንደማንኛውም ቁሳዊ ንብረት ሁሉ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ባለመብቶች የሚሰጡ የባለቤትነት መብቶች መሆናቸውን እንረዳለን። ለዚህም እንደ ምክንያት የሚቀርበው እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ ወጥ ሥራዎችን ለማመንጨት የፈጠራ ባለመብቶች ዕውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውንና ጊዜያቸውን መስዋዕት በማድረግ ከብዙ ድካም በኋላ ያገኟቸው የፈጠራ ውጤቶች በመሆናቸው ነው። ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ ለምን አስፈለገ? አንድም፤ የሰው ልጅ ቀጣይ ዕድገትና የኑሮ ደኅንነት ዋስትና መሠረት የሚያርፈው በቴክኖሎጂና ባሕል ዘርፎች በሚያሳርፋቸው ፈጠራዊ ብቃቶቹ በመሆኑ እንዲሁም የምርምርና የፈጠራ ሥራዎችን ለማካሄድ ተጨማሪ ሀብት የሚያስገኝ በመሆኑና ይህም የኢኖቬሽን ሥርዓቱን ስለሚያሳድግ ነው ይላሉ አቶ ብሩክ። እንዲሁም፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃና ዘርፉን ለሕዝብ የማስተዋወቅ ተግባር ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማረጋገጥ የድርሻውን ስለሚወጣና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት በአጠቃላይ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ በተሻለ ደረጃ ላይ እንዲቆም ስለሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም፤ ሀገራት ጠንካራ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠሩ ቁጥር ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ የልማት መሣሪያ መሆኑን ይገነዘባሉ። ጠንካራና ፍትሐዊ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠራ ባለቤቶችና በተጠቃሚው ሕዝብ ዘንድ ሚዛናዊ ነው ያሉት አቶ ብሩክ። በአጠቃላይ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን በአጽነዖት አንስተዋል። ዜጎች በአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት እንዴት ተጠቃሚ ይሆናሉ? ባለብዙ ቢሊየን ዶላር የፊልምና ድምጽ ሪከርድስ አሳታሚዎችና ሶፍትዌር ኢንዱስትሪዎች ለብዙ ሚሊየኖች የመዝናኛ ሥራዎች የሚያበረክቱት የቅጅ መብት ጥበቃ በመኖሩ መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አቶ ብሩክ ይናገራሉ። በሌላ በኩል ተጠቃሚዎች የሚፈልጓቸውን ምርቶችና አገልግሎቶችን መለየት የሚያስችላቸው ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ የንግድ ምልክቶች ጥበቃና የመብት ማስከበር ሥርዓቶች ባይኖሩ ኖሮ ተመሳስለው በሚቀርቡ ምርቶችና አገልግሎቶች መታለልና ሌሎችም ችግሮች ያጋጥማቸው እንደነበርም ጠቁመዋል። ስለዚህ ምርቶችን በመሸመት ሂደትም በምርቶችና አገልግሎቶች ላይ ያለምንም ግራ መጋባት ግብይቱን ማከናወን እንደሚያስችላቸው መገንዘብ ይቻላል። እንደ አቶ ብሩክ ገለጻ፤ ለፓተንት የፈጠራ ሥራዎች ጥበቃ በመደረጉ መሰጠት የሚገባቸው ማበረታቻዎች የማይሰጡ ከሆነ፤ የፈጠራ ባለሙያዎች ቀጣይ የምርምር ሥራዎችን ማሳደግና ማስፋት እንደማይችሉ ይገመታል። በቀጣይነት የሚገኙ የተሻሻሉ የፈጠራ ሥራዎች አለመኖራቸው ደግሞ፤ በምርቶች ተጠቃሚና አጠቃላይ የኑሮ መሻሻል ሂደት ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተፅዕኖ ይኖረዋል። የአዕምሯዊ ንብረት ዓይነቶች እንዴት ይመደባሉ? የአዕምሯዊ ንብረት፤ የኢንዱስትሪያዊ ንብረት (Industrial Property) እና የቅጅና ተዛማጅ መብቶች (Copyright and Related Rights) በሚሉ ሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚመደብ ያስረዳሉ። አክለውም፤ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት በውስጡ፤ የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ የኢንዱስትሪያዊ ንድፍ እና የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች የተሰኙ አራት ክፍሎችን እንደሚይዝ ያብራራሉ። ፓተንት ምንድን ነው?፡- ፓተንት ማለት በአንድ ቴክኒካዊ ባሕርይ ባለው የፈጠራ ሥራ ላይ የሚኖር የፈጠራ ባለቤትነት ብቸኛ መብት መሆኑን አቶ ብሩክ አስረድተዋል። የፓተንት መብት በአንድ ምርት (ለምሳሌ ማሽን ወይም የአመራረት ሂደት (Process) ሊሰጥ የሚችል ሲሆን፤ ፈጠራውም ለአንድ ቴክኒካዊ ችግር መፍትሔ የሚያስገኝ መሆን ይኖርበታል ይላሉ። ከፈጠራ ሥራው አመንጪ ይሁንታ ውጭ ሥራውን ገበያ ላይ ማዋል፣ መጠቀም፣ ማሰራጨት፣ መሸጥ ወዘተ… እንደማይቻልም አክለዋል። ፓተንት ለባለ መብቱ የጥበቃ መብት የሚያስገኝ ሲሆን፤ የጥበቃው ዘመንም በአጠቃላይ እስከ 20 ዓመት ሊደርስ ይችላል። ፓተንት የሚያስገኛቸው ሕጋዊ (የጥበቃ) መብቶች፡- የፈጠራ ሥራውን መጠቀም የሚችሉና የማይችሉ ሰዎችን መወሰን፤ ሦስተኛ ወገኖች ሥራውን እንዲጠቀሙ የመፍቀድ ወይም የፈቃድ ውል ስምምነት የመስጠት እንዲሁም የፈጠራ ሥራውን የመሸጥ (ለአዲስ የፓተንት ባለመብት) የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል ሥራ አስፈጻሚው። የፓተንት ሥራዎች ለምን ያስፈልጋሉ?፡- ይህን ሲያብራሩም፤ ፓተንት ለፈጠራ ባለመብቶች ዕውቅናንና ሽልማቶችን (ማበረታቻዎችን) የሚሰጥ በመሆኑ፣ ፈጠራዎቹ የኢኖቬሽን ሥራዎችን ስለሚያጠናክሩና በዚህም ቀጣይነት ያለው የሰው ልጅ ሕይወት መሻሻልን የሚያረጋግጥ በመሆኑ እና በሌሎችም በጎ አስተዋጽዖዎች ፓተንት በዕጅጉ አስፈላጊ ነው ብለዋል። የንግድ ምልክት ምንድን ነው?፡- የንግድ ምልክት ማለት አንድን ምርት ወይም አገልግሎት ከሌላው ምርትና አገልግሎት እንዲለይ ለማስቻል በንግድ ምልክት ባለቤቶች ለምርታቸውና አገልግሎታቸው መለያ እንዲሆን ጥቅም ላይ የሚውል ልዩ ምልክት መሆኑን ተናግረዋል። የንግድ ምልክት ሸማቹ ሕብረተሰብ የሚፈልገውን ምርትና አገልግሎት በቀላሉ ለይቶ እንዲገዛ ከማስቻሉም በላይ በሚገዛው ምርትና አገልግሎት ጥራት ላይ በመተማመን ፍላጎቱን እንዲያሟላ ያደርጋል። የንግድ ምልክት ለባለመብቱ ምን ጥቅም ያስገኛል?፡- ምርቶቹ (አገልግሎቶቹ) በተጠቃሚዎች እንዲለዩለት ወይም እንዲታወቁለት ያደርጋል፣ ክፍያን መሠረት አድርጎ ሦስተኛ ወገን እንዲጠቀምበት የመፍቀድ፣ የንግድ ምልክቶች በራሳቸው ዋጋ አላቸው (የአዕምሯዊ ንብረት ዋጋ ትመና (IP Valuation) ለምሳሌ በፈረንጆቹ በ2026 የመጀመሪያ ወራት አፕል (Apple) 600 ቢሊየን ዶላር፣ ማይክሮሶፍት (Microsoft) 565 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር፣ ጉግል (Google) 433 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ዋጋ ግምት እንደነበራቸው ተብራርቷል። በተጨማሪም፤ የንግድ ምልክት በሕግ በሚቀመጥ የጊዜ ገደብ መሠረት እየታደሠ ለዘላለም ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል፤ የንግድ ምልክት ባለቤቱን በማስተዋወቅ ዕውቅናና የገንዘብ ትርፍን ያስገኛል፤ የንግድ ምልክት ተገቢ ያልሆኑ የንግድ ውድድሮችን በመግታት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል (ተመሳስለው የሚሠሩና ለገበያ የሚቀርቡ ሥራዎችን (Counterfieited Products) ለመዋጋት ዓይነተኛ መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል፤ የንግድ ምልክት ሰዎች ምርቶቻቸውንና አገልግሎቶቻቸውን ሚዛናዊ በሆነ አግባብ እንዲያቀርቡ በማድረግና በብሔራዊና ዓለም አቀፍ ደረጃ የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት እንዲኖር ምቹ ሁኔታ በመፍጠር አስተዋጽዖው የላቀ ነው ብለዋል። ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ምንድን ነው?፡- ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ በምርቶች ሥነ-ውበት (Esthetics) ላይ ተመስርቶ ቅርጽን፣ መስመሮችን ወይም ቀለምን በመጠቀም ለገበያ የሚቀርቡ ምርቶች የገዥዎችን (ሸማቾችን) ቀልብ ለመሳብ እንዲችሉ በምርቶች ላይ የሚገለጽ የንድፍ ጥበብ ዘርፍ ነው ያሉት አቶ ብሩክ፤ ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች በኢንዱስትሪና ዕደ-ጥበብ ምርቶች ላይ ተዘጋጅተው ሊወጡና ለገበያ ሊቀርቡ ይችላሉ ይላሉ። ዘርፉ ከቴክኒካልና ሕክምና መሣሪያዎች አንስቶ እንደ ሠዓት፣ ጌጣጌጦችና ሌሎች የቅንጦት ምርቶች ዕቃዎችን ሊያካትት ይችላልም ብለዋል። የቤት ዕቃዎችን፣ የኤሌክትሪክ መሣሪያዎችን፣ ተሽከርካሪዎችና የሕንጻ ንድፎችን እንዲሁም የጨርቃጨርቅ ንድፍ ውጤቶች በኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ሥር የሚወድቁ ይሆናሉ ይላሉ። ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች ጥበቃ የሚደረግላቸው አዲስ ወይም ወጥ ከሆኑ ብቻ መሆኑን ገልጸው፤ በዲዛይኑ ውስጥ ከሚገለጸው ምርት ጋር ተያያዥ የሆኑ የቴክኒክ ጉዳዮች ጥበቃ እንደማይደረግላቸው አስታውቀዋል። ለኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ጥበቃ ማድረግ ለምን ያስፈልጋል?፡- በምርቶች ውበት ላይ የሚገለጽ በመሆኑ የተጠቃሚውን ዐይን ይስባል፣ የምርቶችን ዋጋ ይጨምራል፣ ፈጠራንና ውድድርን ያበረታታል፣ ለባለመብቱ ብቸኛ መብትን ያጎናጽፋል፣ በኢንዱስትሪዎች፣ ባሕላዊ ጥበብና በዕደ ጥበብ ዘርፍ ፈጠራ በማሻሻል ኢኮኖሚ እንዲያድግ ያደርጋል፣ የወጭ ንግድን (Export Trade) ያሳድጋል በማለት የኢንዱስትሪ ንድፍ ጥበቃ አስፈላጊነትን ያብራራሉ። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካች ምንድን ነው?፡- የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች በምርቶች ላይ የሚቀርቡ ምልክቶች ሆነው እነዚህ ምልክቶች አንድ የተወሰነ አካባቢን በምርቱ ምንጭነት የሚያመላክቱና ጥራትንና ዝናን ከቦታው ጋር አስተሳስረው የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን አቶ ብሩክ ያስረዳሉ። በአብዛኛው የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች ልዩ ምርቱ የሚገኝበትን የቦታ ስም (Specific Local Geographyical Factors – Climate, Soil) ይይዛሉ። ለምሳሌ፡- Roquefort for Cheese -France፣ የማረቆ በርበሬ፣ የሸኖ ቅቤ፣ የዓድኣ ጤፍ … የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሾች ናቸው። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾችን መጠበቅ ለምን ያስፈልጋል?፡- ተጠቃሚዎች ምርቶች የሚገኙበትን ሀገር ወይም አካባቢ በቀላሉ ለመለየት፣ ሕጋዊነት በሌላቸው ወገኖች የምርቱ መገኛ አካባቢ እና የምርቱ ዝና በተሳሳተ መልኩ ለሌላ ምርት መጠሪያ እንዳይውል ለመከላከል ይረዳል ይላሉ። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምንድን ናቸው?፡- የቅጅ መብት በሥነ-ጽሑፍ እና ሥነ-ጥበብ ዘርፍ ወጥ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ደራስያን፣ አርቲስቶች ወዘተ… የባለቤትነት መብት የሚሰጥ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑንም ነው ሥራ አስፈጻሚው የሚያስረዱት። በአንጻሩ ተዛማጅ የቅጅ መብት ማለት ይላሉ አቶ ብሩክ፤ በወጥ የፈጠራ ሥራዎች ላይ ተመስርተው የሚሠሩ ተዛማጅ (Related) የፈጠራ ሥራዎችን ያካትታል። ለምሳሌ፡- ከዋኞቹ (ተዋንያን እና ዘፋኞች)፣ ድምጽ ሪከርዲንግስ፣ አሳታሚዎች (ኮምፓክት ዲስኮች)፣ የብሮድካስት ተቋማት፣ (ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን) የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ዘርዝረዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምን ዓይነት መብቶች ያስገኛሉ?፡- ባለመብቶች ሥራዎቻቸውን ለመጠቀም ወይም ሦስተኛ ወገኖች እንዲጠቀሙባቸው የመፍቀድ፣ ሥራዎች እንዲባዙ፣ ለሕዝብ እንዲዳረሱ፣ እንዲሠራጩ፣ እንዲተረጎሙ ወይም ወደሌላ ሥራ እንዲቀየሩ የመፍቀድ ወይም የመከልከል፣ የደራሲነት (የአመንጭነት) መብት ዕውቅና እንዲያገኙ፣ በብዕር ስም የመጠቀም መብት፣ ክብሩንና መልካም ስሙን የሚያጎድፍ የሥራ መዛባት እንዳይኖር የመጠበቅ ወይም የሥራው ወደሌላ መቀየር የሚያስከትለውን ጉዳት የመቃወም ወዘተ መብቶችን ያስገኛሉ ብለዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ምን ጥቅሞች ያስገኛል?፡- የሰውን ልጅ የፈጠራና ኢኖቬሽን ጥረቶችን ያሳድጋል፣ ለፈጠራ አመንጭዎች መበረታታትን ይፈጥራል፣ የሕጋዊ ተፈጻሚነትን በማረጋገጥ አመንጭዎችና በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች መዋዕለ-ነዋይ እንዲያፈሱ የፈጠራ ሥራዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚኖራቸውን የሥርጭት ሽፋን ያሳድጋል ነው ያሉት አቶ ብሩክ። የፓሪስ ስምምነት አባል ኢትዮጵያ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር ለመሆን ለዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት (WIPO) ያስገባችው ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስምምነቱን ነሐሴ 9 ቀን 2017 ዓ.ም በማጽደቁ ከዚሁ ዕለት ጀምሮ ለስምምነቱ ተገዢ ሆናለች። አቶ ብሩክ እንዳብራሩት፤ የፓሪስ ስምምነት በጥቅሉ የኢንዱስትሪያዊ ንብረቶችን ጥበቃ የሚመለከት ነው። የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ፣ የግልጋሎት ሞዴል (በአንዳንድ ሀገራት ሕግ ኢትዮጵያን ጨምሮ “የአነስተኛ ፈጠራ የባለቤትነት መብት” በመባል የተደነገገ)፣ የአገልግሎት ምልክት፣ የንግድ ስም (የኢንዱስትሪ ወይም የንግድ እንቅስቃሴ የሚካሄድባቸው ስያሜዎች)፣ ጂኦግራፊያዊ አመላካች እና ፍትሐዊ ያልሆነ ውድድርን መከላከል ያካተተ ነው። የስምምነቱ መሠረታዊ ድንጋጌዎች በሦስት ዋና ዋና መርሆዎች እንደሚከፈሉ ጠቁመው፤ እነሱም፡- የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር መሆን በሌሎች አባል ሀገራት ውስጥ እንደ ዜጋ የመስተናገድ መብት፣ የቀዳሚነት መብት የማግኘት፣ በቀላሉ ዓለም አቀፍ ጥበቃ የማግኘት አሠራር እና መሰል ጉልህ ጥቅሞችን የማግኘት ዕድል ይሰጣል ሲሉ ይገልጻሉ። በመሠረቱ የፓሪስ ስምምነት የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃን በማቀላጠፍ አዳዲስ ግኝቶችንና ፈጠራዎችን እንዲሁም የንግድ ሥራዎች ድንበር ሳይገድባቸው የፓተንትና የንግድ ምልክት መብቶች በቀላሉ እንዲጠበቁ በማድረግ ፈጠራን፣ ንግድን እና ኢኮኖሚያዊ እድገትን እውን ያደርጋል ብለዋል። የዘንድሮው የአዕምሯዊ ንብረት ቀን የፊታችን ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም “አዕምሯዊ ንብረትና ስፖርት፤ እንዘጋጅ፣ እንጀምር፣ እንፍጠር!” በሚል መሪ ሐሳብ ዓለም አቀፉ የአዕምሯዊ ንብረት ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል። በስፖርት ዓለም ውስጥ የሚከሰቱ ተወዳዳሪዎች የግልና የጋራ ፈጠራዎች፣ ንድፎች፣ ብራንዶችና የመልካም ዝና ታሪኮችን ለመጠበቅና ሀገራትን ጭምር ለማስተዋወቅ የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃ ሥርዓት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል። ምክንያቱም ስፖርት በባሕርይው በውድድር ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን፤ ከሀገራት ዝና፣ ከፋሽን ዲዛይን፣ ከመዝናኛ፣ ከሚዲያ ሥርጭት፣ ከጤናና ከዕለት ተዕለት መገልገያ ቁሶች ጋር የሚገናኝ በመሆኑ ነው።  
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 967
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ ‎በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ‎ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3928
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2683
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8469
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6957
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60918
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54926
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35417
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33034
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 28011
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27291
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26782
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26325
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60918
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54926
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35417
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33034
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 187
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው።   በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል።   የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል።   የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል።   ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 558
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም