ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ አብሮነትና ወንድማማችነትን ያጎለብታሉ
Feb 26, 2026 15
ወልቂጤ ፤የካቲት 19/2018(ኢዜአ) :- ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ አብሮነትና ወንድማማችነትን ለማጎልበት እንደሚያስችሉ ተመላከተ። በወልቂጤ ከተማ ለተከታታይ 10 ቀናት ሲካሄድ የቆየው 3ኛው የክልል አቀፍ ሻምፒዮናና የባህል ስፖርቶች ውድድር ፌስቲቫል ተጠናቋል፡፡ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሶ፤ በወቅቱ እንዳሉት ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ አብሮነትና ወንድማማችነትን ያጎለብታሉ።   በ17 ዘርፎች የተካሔደው ስፖርታዊ ውድድሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመወዳደር የሚችሉ ስፖርተኞች የተለዩበት እንደሆነም ገልፀዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ በዋናነትም በዘርፉ የወጣቶችን ተሰጥኦ ለመለየት እገዛው የጎላ እንደነበርም ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት በዘርፉ የሚፈገለውን ውጤት ለማምጣት የስፖርት ማዘውተሪያ መሰረተ ልማቶችን ከመገንባት ባሻገር ስፖርታዊ ጨዋነትን የሚያሳድጉ ተግባራት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው፣ መርሃ ግብሩ የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን በማጎልበት በተሻለ መንገድ አንድነትን ለመፍጠር ያስቻለ መሆኑን ጠቅሰዋል።   ስፖርታዊ ውድድሩ በአካባቢው ላይ መነቃቃትን የፈጠረ ሲሆን የባሕል እሴቶችንም ለማስተዋወቅ ትልቅ እገዛ አድርጓል ነው ያሉት። ታዳጊ ወጣቶችን ለማፍራት የተከናወኑት ተግባራት አዳዲስ እና ተተኪ ስፖርተኞች የተገኙበት መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ የስፖርት ትምህርት ስልጠና ባለሙያ አቶ ባዘዘው ደምሴ ናቸው ። በዞኑ በተዘጋጀው የውድድር መርሃ ገብር ላይ በ17 ዓይነት የውድድር ዘርፎች ተወዳዳሪዎችን ማሳተፍ መቻሉን ጠቅሰው ይህም መንግስት ለስፖርቱ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት ያመላክታል ብለዋል። የጠንባሮ ልዩ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት የስፖርት ተሳትፎና ውድድር ቡድን መሪ አቶ አባይነህ ጎበዜ በበኩላቸው፤ በክልሉ በስፖርት ዘርፍ የተጀመረውን ሥራ ለማጠናከር እየተደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ከክልል ጀምሮ በየደረጃው ያሉ ኃላፊዎችና የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በስፖርታዊ ውድድሩ የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች የሜዳሊያ፣ የዋንጫና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።
በሁሉም የልማት መስኮች የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን ያፋጠኑ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Feb 26, 2026 34
ቦንጋ/ሚዛን፤የካቲት19/2018 (ኢዜአ)፡-ብልጽግና ፓርቲ በሁሉም የልማት መስኮች የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ስኬቶችን በተግባር ማስመዝገቡ ተገለጸ። ፓርቲው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን የስንዴ ነዶ እና ማኒፌስቶውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሚዛን አማን እና ቦንጋ ከተሞች ዛሬ ለህዝብና ለደጋፊዎቹ አስተዋውቋል። በቦንጋ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ፣ ብልጽግና ባለፉት ዓመታት እዳን ወደ ምንዳ በመቀየር በፈጠራና በፍጥነት እሳቤ ሀገራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ እየተጋ ያለ ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው የተከተለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕሳቤ ኢትዮጵያ ከምትታወቅበት ድህነት ወጥታት በልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ለመሸጋገር የሚያስችላት መሆኑን ጠቅሰዋል። በፓርቲው መሪነት ባለፉት ዓመታት በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በቴክኖሎጂና በኢንዱስትሪ ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስኬቶች መመዝገባቸውንና ይህም ተጠናከሮ መቀጠሉን ነው የተናገሩት። በማህበራዊ ዘርፍም ሰው ተኮር የልማት ሥራዎችን በማከናወን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ ትችሏል ብለዋል። በዞኑ ሰፊ የልማት ሀብት ቢኖርም ትኩረት ባለመሰጠቱ ህዝቡ ተጠቃሚ ሳይሆን ቆይቷል ያሉት አስተዳዳሪው፣ በፓርቲው መሪነት በዞኑ ልማትን ለማፋጠን በተሰራው ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል። የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነው የስንዴ ነዶ የአብሮነት፣ የጥንካሬ፣ የአንድነትና በምግብ ራስን የመቻል መሆኑን ጠቁመው፣ ፓርቲውን መምረጥ ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ማስቀጠል ነው ብለዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የካፋ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ ሀይሌ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ብልፅግና ፓርቲ እንደሀገር የገጠሙ ስብራቶችን በመጠገንና ልማትን በማስቀጠል ዜጎችን ተጠቀሚ እያደረገ ይገኛል። በካፋ ዞን ሁለንተናዊ ለውጥ ለማስመዝገብ በትኩረት በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት እየመጣ ነው ያሉት ሀላፊው፣ በዚህም የዞኑ ነዋሪዎች ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መጥቷል ብለዋል። ዞኑ በልማት ወደኋላ ቀርቶ እንደነበረ አቶ አጥናፉ አስታውሰው፣ በፓርቲው መሪነት ይህን ለመቀየር የተወሰደ እርምጃ ህዝብን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።   በተመሳሳይ ዜና በሚዛን አማን ከተማ በተከሄደ መድረክ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን እንዳሉት ፓርቲው የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ሥራዎችን በተጨባጭ እያከናወነ ይገኛል። ምርጫ ለአንድ ሀገር ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ በመሆኑ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።   በፓርቲው መሪነት ባለፉት የለውጥ ዓመታት በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችና አዳዲስ እሳቤዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ የልማት ተምሳሌት የሚያደርጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። "ብልጽግና የሕዝብ ተጠቃሚነትን ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ሥራዎችን በተጨባጭ ያስመዘገበና ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን ዓልሞ የሚሰራ ነው" ሲሉ አክለዋል። ዞኑ ከሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት ተጠቃሚ መሆኑን የገለጹት አስተዳዳሪው፣ በብዝሃ ኢኮኖሚ እይታ የተገነባው የደንቢ ኢኮ ሎጅ ለዚህ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል ፓርቲው ድህነትን ለማሸነፍ በግብርና ዘርፍ የጀመራቸው ኢኒሼቲቮች ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበባቸው በመሆኑ የማኅበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ነው ብለዋል። ብልጽግና የኢኮኖሚ አማራጭ መፍጠሩ በአካባቢያችን ያሉ አንጡራ ሀብቶችን አውጥቶ ለመጠቀም አስችሏል ያሉት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የቤንች ሸኮ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኩድን ናቸው። በቦንጋና በሚዛን አማን ከተማ በተካሄዱ መድረኮች የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የህብረተሰብ ተወካዮች፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።      
ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከአጋር አካላት ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ ነው
Feb 26, 2026 43
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከአጋር አካላት ጋር የተቀናጀ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በካንሰር ምርምር ላይ የሚያተኩረውን የelse korner center fore cancer care (EKC 2) ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍን በመጠናቀቅ ሁለተኛውን ምዕራፍ ይፋ አድርጓል፡፡   ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት ለቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚተገበር ሲሆን የሴቶችን የካንሰር ሕክምና አገልግሎት በየአካባቢው ተደራሽ ማድረግ፣ ስለ ጡት እና ማህፀን በር ካንሰር ግንዛቤን ማሳደግ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሕይወት ሰለሞን በዚሁ ወቅት፤ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ከመከሰታቸው በፊት በቅድመ ጥንቃቄ መከላከል ይቻላል ብለዋል፡፡ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በሰዎች ላይ የሚያስከትሉትን ማኅበራዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ለመግታት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል፡፡ መንግስት የበሽታዎቹን ስርጭት ለመግታት ከግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ባሻገር ሌሎች ውጤታማ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ህብረተሰቡ የሚያደርገውን ጥንቃቄ ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የካንሰርና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርምር ክፍል አስተባባሪ ዶክተር አዳሙ አዲሴ በበኩላቸው፤ የካንሰር በሽታ በአፍሪካ ደረጃ አሳሳቢነቱ እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመዋል። ይህንን ለመቅረፍ ኮሌጁ ችግር ፈቺ በሆኑ ምርምሮች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑንና የኤልሳ ክሮነር የካንሰር ሕክምና ማዕከል ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ገልጸዋል።   የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ የጤና ማጎልበትና በሽታ መከላከል ዳይሬክተር አቶ ጌቱ ቢሳ እንደገለጹት፣ ፕሮጀክቱ በተለይ በእናቶች ላይ የሚከሰቱ የጡትና የማህፀን በር ካንሰር ለመቀነስ ትልቅ ሚና አለው። ቀደም ሲል በተመረጡ ሆስፒታሎች ብቻ ይሰጥ የነበረው አገልግሎት አሁን በፕሮጀክቱ አማካኝነት ወደ ጤና ጣቢያዎች ዝቅ እንዲል መደረጉንም ጠቅሰዋል፡፡
ወላይታ ድቻ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ 
Feb 26, 2026 40
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ጨዋታዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ወላይታ ድቻ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። ካርሎስ ዳምጠው ግቦቹን አስቆጥሯል። የድሬዳዋ ከተማው ድልአዲስ ገብሬ በ51ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። በሊጉ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ወላይታ ድቻ በ22 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በሊጉ አራተኛ ደረጃን ይዟል። በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ25 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሐ ግብር አዳማ ከተማ እና ሸገር ከተማ ሶስት አቻ ተለያይተዋል።   ለአዳማ ከተማ አላዛር ሽመልስ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር አህመድ ሁሴን ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጀቤሳ ሚኤሳ እና ቢንያም ፍቅሩ በጨዋታ ሄኖክ አዱኛ በፍጹም ቅጣት ምት ለሸገር ከተማ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። አዳማ ከተማ በ32 ነጥብ አምስተኛ፣ ሸገር ከተማ በ23 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዘዋል።
የሚታይ
ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከአጋር አካላት ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ ነው
Feb 26, 2026 43
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከአጋር አካላት ጋር የተቀናጀ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በካንሰር ምርምር ላይ የሚያተኩረውን የelse korner center fore cancer care (EKC 2) ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍን በመጠናቀቅ ሁለተኛውን ምዕራፍ ይፋ አድርጓል፡፡   ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት ለቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚተገበር ሲሆን የሴቶችን የካንሰር ሕክምና አገልግሎት በየአካባቢው ተደራሽ ማድረግ፣ ስለ ጡት እና ማህፀን በር ካንሰር ግንዛቤን ማሳደግ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሕይወት ሰለሞን በዚሁ ወቅት፤ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ከመከሰታቸው በፊት በቅድመ ጥንቃቄ መከላከል ይቻላል ብለዋል፡፡ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በሰዎች ላይ የሚያስከትሉትን ማኅበራዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ለመግታት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል፡፡ መንግስት የበሽታዎቹን ስርጭት ለመግታት ከግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ባሻገር ሌሎች ውጤታማ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ህብረተሰቡ የሚያደርገውን ጥንቃቄ ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የካንሰርና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርምር ክፍል አስተባባሪ ዶክተር አዳሙ አዲሴ በበኩላቸው፤ የካንሰር በሽታ በአፍሪካ ደረጃ አሳሳቢነቱ እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመዋል። ይህንን ለመቅረፍ ኮሌጁ ችግር ፈቺ በሆኑ ምርምሮች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑንና የኤልሳ ክሮነር የካንሰር ሕክምና ማዕከል ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ገልጸዋል።   የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ የጤና ማጎልበትና በሽታ መከላከል ዳይሬክተር አቶ ጌቱ ቢሳ እንደገለጹት፣ ፕሮጀክቱ በተለይ በእናቶች ላይ የሚከሰቱ የጡትና የማህፀን በር ካንሰር ለመቀነስ ትልቅ ሚና አለው። ቀደም ሲል በተመረጡ ሆስፒታሎች ብቻ ይሰጥ የነበረው አገልግሎት አሁን በፕሮጀክቱ አማካኝነት ወደ ጤና ጣቢያዎች ዝቅ እንዲል መደረጉንም ጠቅሰዋል፡፡
ኢትዮጵያ የገነባችው አስተማማኝ ሠራዊት በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና ነው
Feb 26, 2026 46
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የገነባችው አስተማማኝ ሠራዊት በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና መሆኑን የቀድሞው የአየር ወለድ አዛዥና ወደር የሌለው የኢትዮጵያ የጦር ሜዳ ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ገለጹ፡፡ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በተከበረበት ወቅት፣ ከኢትዮጵያ ባለፈ የቀጣናውንና የአፍሪካን ነጻነትና ሰላም ዛሬም እንደትናንቱ የሚያስከብር አስተማማኝ ኤሊት ፎርስ ተገንብቷል ብለዋል፡፡ የሠራዊቱ የተሟላ ዝግጁነት በድፍን አፍሪካ ሰላም እና ብልጽግናን ለማረጋገጥ በቀጣናው ላሉ ሀገራትም አለኝታና መከታ እንደሚሆን ገልጸዋል። የቀድሞው የአየር ወለድ አዛዥና ወደር የሌለው የኢትዮጵያ የጦር ሜዳ ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ወታደራዊ ሳይንስን፣ ስነ-ልቦናዊ ግንባታን እና የአካል ብቃትን መሠረት አድርጎ የተገነባ ሠራዊት ለሀገር ህልውና ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ስልጠና የድል በር መክፈቻ ቁልፍ ነው ያሉት ብርጋዴር ጀነራሉ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለችው ሠራዊት ጥራት ያለው፣ በሁሉም መልኩ የተዘጋጀ አስተማማኝ ኃይል መሆኑን ገልጸዋል።   በ65ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የምስረታ በዓል የተመለከቱት የሠራዊቱ ትርኢትም በሁኔታዎች የማይበገር ወሳኝ ኃይል መገንባቱን ያሳየ ነው ብለዋል። "በሕይወት ኖሬ የኢትዮጵያ ሠራዊት በዚህ መልኩ ተገንብቶ በማየቴ እንደገና እንደተወለድኩ ነው የቆጠርኩት" ሲሉም ነው የገለጹት። ኢትዮጵያ አሁን ላይ የገነባችው ኃይል የራሷን ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ ባለፈ የአካባቢው ሀገራት ጭምር የሚታመኑበትና ዋስትና የሚሆናቸው ኃይል ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን ሠራዊት ቁመና እና ጥንካሬ ያደነቁት ብርጋዴር ጀኔራሉ፥ ይህም ሀገራችን በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና መሆኑን ገልጸዋል። ሠራዊቱ ሁሉንም አቀፍ እውቀትና ዘመናዊ ትጥቅ የታጠቀ በመሆኑ በአየር፣ በባህር፣ በየብስ እንዲሁም በየትኛውም አውድና የመሬት ገፅ ድል አብሳሪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ብርጋዴር ጀኔራል ተስፋዬ አክለውም ኢትየጵያ ተግባርና ኃላፊነቱን ጠንቅቆ የሚያውቅ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸና ከራሷ አልፎ ለአፍሪካውያን ሠላም ዋስትና የሚሆን ሠራዊት መገንባቷን አመልክተዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምጽዋ ጫፍ በባህር ላይ የሚያጋጥሙ ሽብሮችን የሚያስቀር ኤሊት ፎርስ መገንባቱን መግለጻቸው ይታወቃል። ተቋም የምንገነባው፣ ኤሊት ፎርስ የምንገነባው፤ በቀጣናችን ውጊያና ሽብር እንዳይፈጠር ነው፤ ሲፈጠርም በአጠረ ጊዜ ለመቋጨት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ይህን አይነት ተቋም በመገንባቷ የምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ሀገራት እንኳን ደስ አላችሁ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የትብብር አድማስ ለማስፋት ትሻለች - አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ
Feb 26, 2026 67
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር በታሪክ እና ባህል ያላትን ትስስር በሌሎች መስኮችም የማስፋት ፍላጎት እንዳላት በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ ገለጹ። አምባሳደር ዮሶን ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ጊዜ የቆየ ትስስር እንዳላቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። የአድዋ ድል በኮሎምቢያ ለሚኖሩ የአፍሮ-ካሪቢያን ዝርያ ላላቸው ዜጎች የክብር እና የተነሳሽነት ምንጭ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በአድዋ ድል የሰብዓዊነት እናት፣ የታጋይነት እና አይበገሬነት ምልክት ሆናለች ሲሉም ነው የተናገሩት። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለተካሄዱ የፀረ-ቅኝ ግዛት እንቅስቃሴዎች ቁልፍ ሚና አላት ብለዋል። የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው የኮሎምቢያ ዜጎች ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸው ትስስር ለሀገራቱ የባህል ትብብር የጠለቀ እንዲሆን አድርጎታልም ነው ያሉት አምባሳደሩ። አምባሳደር ዬሰን የኮሎምቢያ እና ኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እያደገ መምጣቱን አንስተው በተለይም ሀገራቱ በቡና ዘርፍ የቴክኒክ ልውውጦች እና የጋራ ውይይቶችን በቋሚነት እያደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ በቡና ምርት ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ ለመከላከል ሀገራቱ በትብብር እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል። ቡና ለሁለቱም ሀገራት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ዘርፍ መሆኑን ጠቁመው ለዜጎች የኑሮ መሻሻል እና የገቢ እድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል። በሌላ በኩል አምባሳደሩ የአዲስ አበባን ፈጣን ለውጥ በማድነቅ ከኮሎምቢያ መዲና ቦጎታ ጋር ያላትን ትብብር አንስተዋል። ቦጎታ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የከተማ ሪፎርሞች ውስጥ ማለፏን አውስተው ሁለቱ ከተሞች ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የከተማ ልማትን ለማስፋት የልምድ ልውውጦችን እያደረጉ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗንም ጨምረው አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ እና ኮሎምቢያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ 1947 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ኮሎምቢያ በነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኤምባሲ ዳግም መክፈቷ የሚታወስ ሲሆን ይህም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
በቱሪዝም ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል
Feb 26, 2026 102
አርባ ምንጭ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ የቱሪዝም ዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ አስታወቁ። የቱሪዝም ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት የዘርፉ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ እንደተናገሩት የቱሪዝም ዘርፍ ለ10 ዓመት የሀገሪቱ የልማት ዕቅድ ስኬት ወሳኝ ድርሻ ያለው በመሆኑ ሚኒስቴሩ የመካከለኛ ዘመን ዕቅድ ነድፎ እየሠራ ይገኛል ብለዋል። በሀገሪቱ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ የቱሪዝም ፀጋዎችን በመጠበቅ፣ በማልማትና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስፋፋት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጀመሩ የገበታ ለሀገርና ለትውልድ ፕሮጀክቶች በአዳዲስ እይታ በዘርፉ ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈቱ ናቸው ብለዋል።   እንደ ሀገር የቱሪዝም ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና ነባሮቹን በማጠናከር ለጎብኚዎች ክፍት መደረጉንና በዚህም ውጤት መገኘቱን ጠቅሰዋል። በርካታ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በተደረጉ ጥረቶች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ጠቅሰው ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ይሰራል ብለዋል። በፈረንጆች 2025 በቱሪዝም ዘርፍ 15 በመቶ ዕድገት መመዝገቡን አስታውሰው፣ ለዚህም የመገናኛ ብዙሃን፣ የግሉ ዘርፍ፣ የልማት አጋሮችና ሌሎች ድርሻቸው ጉልህ እንደነበር ተናግረዋል። በቀሪ ወራትም በየደረጃው ያሉ ተቋማትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማጠናከር፣ ብቁ አመራሮችና ባለሙያዎችን ለመፍጠርና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት ይሠራል ነው ያሉት። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ቱሪዝም ከብዝሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ አምዶች መካከል ለብልጽግና ጉዞ ስኬት አይተኬ ሚና እንዳለው አንስተዋል። በክልሉም ሰፊ የቱሪዝም አቅም እንዳለ ጠቁመው፤ በተለይ የረጅም ጊዜ የታሪክ፣ የድንቅ ባህል፣ የተፈጥሮ ሀብት እንዲሁም የብዝሃነት ፀጋ ባለቤት መሆኑ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ አቅም ነው ብለዋል። ከክልሉ በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቅርሶች፣ ብሔራዊ ፓርኮች እንዲሁም ባህላዊ፣ ተፈጥሯዊና ሃይማኖታዊ የቱሪዝም ሀብቶች ለሀገሪቱ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የመስህብ ስፍራዎቹን በማልማት፣ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በማስፋፋትና ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማላቅ የክልሉ መንግስት በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል ነው ያሉት። አርባ ምንጭ ከተማ በቱሪዝም ሀብቷና በሰላም እሴቷ የደመቀች በመሆኗ ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላት የገለጹት ደግሞ የከተማዋ ከንቲ መስፍን መንዛ(ዶ/ር) ናቸው። በከተማዋ እየተገነባ ያለው የገበታ ለትውልድ ኮንፍረንስ ሪዞርት ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ጠቅሰው፣ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ አበርክቶ ከፍ ለማድረግ እየተሠራ ነው ብለዋል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ አባላትን ጨምሮ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደር የዘርፉ ተጠሪዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አገልግሎቶቹን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ አድርጓል
Feb 26, 2026 98
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ሥርዓት ለማቀላጠፍና ቁጥጥሩን ለማዘመን አገልግሎቶቹን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማድረጉን የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ። ኢትዮጵያ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ በርካታ ውጤታማ የዲጂታላይዜሽን ተግባራትን አከናውናለች። ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችለው ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ዲጂታል ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ነው በዲጂታል 2025 በርካታ ተቋማት አገልግሎታቸውን ያዘመኑ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በዲጂታል የተደገፈ የተቀላጠፈ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ። የጉምሩክ ኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ ዲጂታል 2025 ተከትሎ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ አተኩሮ በርካታ ውጤታማ ተግባራት በማከናወን የሚሰጡ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ ተችሏል፡፡፡ በአሁኑ ወቅት ነጋዴዎች በማንኛውም ቦታ ሆነው የጉምሩክ ሥርዓትን መፈጸም የሚችሉበት የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት መዘርጋት መቻሉን አስታውቀዋል። ከ70 በላይ ተቋማትን በአንድ ላይ የሚያገናኘው የኤሌክትሮኒክ ሲንግል ዊንዶው ፕላትፎርም ተግባራዊ መድረጉን አንስተው፤ ይህም የንግድ ስራን ለማቀላጠፍ ትልቅ እመርታ መሆኑን ተናግረዋል። የኮሚሽኑን የክትትል አቅም ለማሳደግ ስማርት ቦርደር ማኔጅመንት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ሲሉም አንስተዋል፡፡ የኤሌክትሮኒክ ካርጎ ትራኪንግ ሲስተምን በመጠቀም ጭነቶች ካለባቸው መስመር እንዳይወጡ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝም ምክትል ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል፡፡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዙ ካሜራዎች በተለያዩ ስልታዊ ቦታዎች ላይ ተተክለው ውጤታማ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ምክትል ኮሚሽነሩ ኮሚሽኑ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ከባንኮችና ከሌሎች ፈቃጅና ተቆጣጣሪ ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂ ትስስር መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡ በሀገር ውስጥ የታክስ ሥርዓትም የኢ-ፋይሊንግ እና የኢ-ፔይመንት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ ውለዋል ብለዋል። እንደ ምክትል ኮሚሽነሩ ገለጻ በአሁኑ ወቅት በጂቡቲ የሚገኙ ሁለት ቅርንጫፎችን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ ያሉ 15 ቅርንጫፎች በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የ24 ሰዓት አገልግሎት በቴክኖሎጂ በመስጠት ላይ ይገኛሉ። ይህ መጠነ ሰፊ የዲጂታላይዜሽን ስራ የገቢና ወጪ ንግዱን ከማሳለጡ ባለፈ፣ የህግ ማስከበር ስራውን በቴክኖሎጂ የታገዘና ግልጽ አሰራረን ተግባራዊ በማድረግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚደግፍ አስታውቀዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በሁሉም የልማት መስኮች የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን ያፋጠኑ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Feb 26, 2026 34
ቦንጋ/ሚዛን፤የካቲት19/2018 (ኢዜአ)፡-ብልጽግና ፓርቲ በሁሉም የልማት መስኮች የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ስኬቶችን በተግባር ማስመዝገቡ ተገለጸ። ፓርቲው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን የስንዴ ነዶ እና ማኒፌስቶውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሚዛን አማን እና ቦንጋ ከተሞች ዛሬ ለህዝብና ለደጋፊዎቹ አስተዋውቋል። በቦንጋ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ፣ ብልጽግና ባለፉት ዓመታት እዳን ወደ ምንዳ በመቀየር በፈጠራና በፍጥነት እሳቤ ሀገራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ እየተጋ ያለ ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው የተከተለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕሳቤ ኢትዮጵያ ከምትታወቅበት ድህነት ወጥታት በልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ለመሸጋገር የሚያስችላት መሆኑን ጠቅሰዋል። በፓርቲው መሪነት ባለፉት ዓመታት በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በቴክኖሎጂና በኢንዱስትሪ ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስኬቶች መመዝገባቸውንና ይህም ተጠናከሮ መቀጠሉን ነው የተናገሩት። በማህበራዊ ዘርፍም ሰው ተኮር የልማት ሥራዎችን በማከናወን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ ትችሏል ብለዋል። በዞኑ ሰፊ የልማት ሀብት ቢኖርም ትኩረት ባለመሰጠቱ ህዝቡ ተጠቃሚ ሳይሆን ቆይቷል ያሉት አስተዳዳሪው፣ በፓርቲው መሪነት በዞኑ ልማትን ለማፋጠን በተሰራው ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል። የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነው የስንዴ ነዶ የአብሮነት፣ የጥንካሬ፣ የአንድነትና በምግብ ራስን የመቻል መሆኑን ጠቁመው፣ ፓርቲውን መምረጥ ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ማስቀጠል ነው ብለዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የካፋ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ ሀይሌ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ብልፅግና ፓርቲ እንደሀገር የገጠሙ ስብራቶችን በመጠገንና ልማትን በማስቀጠል ዜጎችን ተጠቀሚ እያደረገ ይገኛል። በካፋ ዞን ሁለንተናዊ ለውጥ ለማስመዝገብ በትኩረት በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት እየመጣ ነው ያሉት ሀላፊው፣ በዚህም የዞኑ ነዋሪዎች ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መጥቷል ብለዋል። ዞኑ በልማት ወደኋላ ቀርቶ እንደነበረ አቶ አጥናፉ አስታውሰው፣ በፓርቲው መሪነት ይህን ለመቀየር የተወሰደ እርምጃ ህዝብን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።   በተመሳሳይ ዜና በሚዛን አማን ከተማ በተከሄደ መድረክ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን እንዳሉት ፓርቲው የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ሥራዎችን በተጨባጭ እያከናወነ ይገኛል። ምርጫ ለአንድ ሀገር ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ በመሆኑ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።   በፓርቲው መሪነት ባለፉት የለውጥ ዓመታት በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችና አዳዲስ እሳቤዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ የልማት ተምሳሌት የሚያደርጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። "ብልጽግና የሕዝብ ተጠቃሚነትን ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ሥራዎችን በተጨባጭ ያስመዘገበና ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን ዓልሞ የሚሰራ ነው" ሲሉ አክለዋል። ዞኑ ከሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት ተጠቃሚ መሆኑን የገለጹት አስተዳዳሪው፣ በብዝሃ ኢኮኖሚ እይታ የተገነባው የደንቢ ኢኮ ሎጅ ለዚህ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል ፓርቲው ድህነትን ለማሸነፍ በግብርና ዘርፍ የጀመራቸው ኢኒሼቲቮች ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበባቸው በመሆኑ የማኅበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ነው ብለዋል። ብልጽግና የኢኮኖሚ አማራጭ መፍጠሩ በአካባቢያችን ያሉ አንጡራ ሀብቶችን አውጥቶ ለመጠቀም አስችሏል ያሉት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የቤንች ሸኮ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኩድን ናቸው። በቦንጋና በሚዛን አማን ከተማ በተካሄዱ መድረኮች የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የህብረተሰብ ተወካዮች፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።      
ኢትዮጵያ የገነባችው አስተማማኝ ሠራዊት በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና ነው
Feb 26, 2026 46
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የገነባችው አስተማማኝ ሠራዊት በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና መሆኑን የቀድሞው የአየር ወለድ አዛዥና ወደር የሌለው የኢትዮጵያ የጦር ሜዳ ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ገለጹ፡፡ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በተከበረበት ወቅት፣ ከኢትዮጵያ ባለፈ የቀጣናውንና የአፍሪካን ነጻነትና ሰላም ዛሬም እንደትናንቱ የሚያስከብር አስተማማኝ ኤሊት ፎርስ ተገንብቷል ብለዋል፡፡ የሠራዊቱ የተሟላ ዝግጁነት በድፍን አፍሪካ ሰላም እና ብልጽግናን ለማረጋገጥ በቀጣናው ላሉ ሀገራትም አለኝታና መከታ እንደሚሆን ገልጸዋል። የቀድሞው የአየር ወለድ አዛዥና ወደር የሌለው የኢትዮጵያ የጦር ሜዳ ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ወታደራዊ ሳይንስን፣ ስነ-ልቦናዊ ግንባታን እና የአካል ብቃትን መሠረት አድርጎ የተገነባ ሠራዊት ለሀገር ህልውና ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ስልጠና የድል በር መክፈቻ ቁልፍ ነው ያሉት ብርጋዴር ጀነራሉ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለችው ሠራዊት ጥራት ያለው፣ በሁሉም መልኩ የተዘጋጀ አስተማማኝ ኃይል መሆኑን ገልጸዋል።   በ65ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የምስረታ በዓል የተመለከቱት የሠራዊቱ ትርኢትም በሁኔታዎች የማይበገር ወሳኝ ኃይል መገንባቱን ያሳየ ነው ብለዋል። "በሕይወት ኖሬ የኢትዮጵያ ሠራዊት በዚህ መልኩ ተገንብቶ በማየቴ እንደገና እንደተወለድኩ ነው የቆጠርኩት" ሲሉም ነው የገለጹት። ኢትዮጵያ አሁን ላይ የገነባችው ኃይል የራሷን ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ ባለፈ የአካባቢው ሀገራት ጭምር የሚታመኑበትና ዋስትና የሚሆናቸው ኃይል ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን ሠራዊት ቁመና እና ጥንካሬ ያደነቁት ብርጋዴር ጀኔራሉ፥ ይህም ሀገራችን በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና መሆኑን ገልጸዋል። ሠራዊቱ ሁሉንም አቀፍ እውቀትና ዘመናዊ ትጥቅ የታጠቀ በመሆኑ በአየር፣ በባህር፣ በየብስ እንዲሁም በየትኛውም አውድና የመሬት ገፅ ድል አብሳሪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ብርጋዴር ጀኔራል ተስፋዬ አክለውም ኢትየጵያ ተግባርና ኃላፊነቱን ጠንቅቆ የሚያውቅ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸና ከራሷ አልፎ ለአፍሪካውያን ሠላም ዋስትና የሚሆን ሠራዊት መገንባቷን አመልክተዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምጽዋ ጫፍ በባህር ላይ የሚያጋጥሙ ሽብሮችን የሚያስቀር ኤሊት ፎርስ መገንባቱን መግለጻቸው ይታወቃል። ተቋም የምንገነባው፣ ኤሊት ፎርስ የምንገነባው፤ በቀጣናችን ውጊያና ሽብር እንዳይፈጠር ነው፤ ሲፈጠርም በአጠረ ጊዜ ለመቋጨት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ይህን አይነት ተቋም በመገንባቷ የምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ሀገራት እንኳን ደስ አላችሁ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በለውጡ መንግስት የተመዘገቡ የልማት ውጤቶች የጌዴኦ ዞን ህዝብን ተጠቃሚ አድርገዋል
Feb 26, 2026 83
ዲላ፣ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡-በጌዴኦ ዞን ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ የተመዘገቡ የልማት ውጤቶች የህዝቡን ተጠቃሚነት በተጨባጥ ያረጋገጡ መሆናቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። ብልጽግና ፓርቲ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ ማኒፌስቶውንና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን የስንዴ ነዶ በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ ለህዝብና ለፓርቲው ደጋፊዎች አስተዋውቋል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት ፓርቲው ሃገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርምን ተግባራዊ በማድረግ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋጋር ተግቶ እየሰራ ነው። በዚህም የጌዴኦ ህዝብ በተለያዩ የልማት ዘርፎች ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ በተለይ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ውጤት አመርቂ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ በቡና ልማት በሄክታር እስከ 19 ኩንታል በማግኝት ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበው ቡና ከ40 ሺህ ቶን በላይ መድረሱን በማሳያነት ጠቅሰዋል። በእንሰትና ፍራፍሬ ልማትም የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻሉን አንስተው ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በፓርቲው መሪነት በዞኑ የመጡ ድሎችን ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የዞኑ ህዝብም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ምርጫው ስላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል።   በከተማው ባለፉት አምስት ዓመታት የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ጨምሮ ከ252 በላይ የልማት ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት በማብቃት ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ መሰጠቱን ያነሱት ደግሞ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ናቸው። በተለይ በከተማው ሁሉንም የመንግስት አገልግሎት በማዘመንና ዲጂታል በማድረግ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ተችሏል ብለዋል። በዚህም የህዝብን የዘመናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት በተሰራው ስራ ውጤት መመዝገቡን ነው ያስታወቁት። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብን ይሁንታ ካገኘ እነዚህን የተመዘገቡ ውጤቶች በማጠናከር ለላቀ የህብረተሰብ ተጠቃሚነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። ‎በብልጽግና ፓርቲ የጌዴኦ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፍት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር ተመስገን ጥላሁን በበኩላቸው ‎ጠቅላላ ምርጫው የፓርቲው የመወዳደሪያ ምልክት የስንዴ ነዶ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻልና የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ በገጠርና በከተማ በተለያዩ መስኮች እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። ‎ በመርሐ ግብሩ ላይ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ወጣቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና በርካታ የፓርቲው ደጋፊዎች ተገኝተዋል።    
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል
Feb 26, 2026 84
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለኢትዮጵያ ዕድገትና ለህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን በሸገር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ። የዘንድሮው ኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ማሳወቁ ይታወቃል። በዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትና ማኒፌስቷቸውን በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። ዜጎችም በመጪው ግንቦት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚችሉበትን ካርድ ለመውሰድ እየተጠባበቁ ይገኛል። የሸገር ከተማ ነዋሪ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለኢዜአ እንዳሉትም፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለህዝብና ለሀገር ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት በማፋጠን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅምና አንድነት ለሚሰራ የፓለቲካ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት በምርጫ ሂደቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ነጋሽ ኢደኦ እንዳሉት፤ ምርጫ ዜጎች ለሀገርና ህዝብ አንድነት ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ የሚመርጡበት ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫም የሀገርን ዕድገት፣ የህዝብን አንድነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትጋት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።   ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ሀዳ ሲንቄ ጫልቱ ቀነዓ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምርጫ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማፋጠን ለሀገር ዕድገት የሚረዳ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣዩ ጠቅላላ ምርጫም የኢትዮጵያን ሰላም፣ ልማትና ዕድገት በማሳለጥ ለዜጎች አንድነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ምርጫ የአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መገለጫ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ድጋፌ ኤዪ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው።   በዚህም በቀጣዩ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቦች ሕብረብሔራዊ አንድነትና ተጠቃሚነት እንዲሁም ለሀገር ዕድገት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል። ዜጎችም ሀገርን በሚገባ በማስተዳደር ዕድገትና ልማትን ያፋጥናል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ምርጫው ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሕዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የማድረግ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።   የሸገር ከተማ ነዋሪ ወጣት ኢፌ ባልቻ በበኩሏ፤ በጠቅላላ ምርጫው ላይ ለሀገርና ህዝብ ይበጃል የምለውን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ ድምጽ ለመስጠት ጊዜውን እየተጠባበኩ ነው ብላለች። በተለይም የኢትዮጵያና የሸገር ከተማን ልማት በማፋጠን የህዝቦች አንድነት፣ የሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ እንደምትሰጥ ገልፃለች። ወጣቶችም በመጪው ግንቦት ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማነት የሚጠበቅባቸውን ገንቢ ኃላፊነት መወጣት እንደሚኖርባቸው ጠቅሳለች።      
ብልጽግና ፓርቲ አካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት በመገንባት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ ይተጋል -የፓርቲው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች
Feb 26, 2026 87
ባህርዳር/ጎንደር/ገንዳ ውሃ/ደብረ ማርቆስ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ አካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት በመገንባት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እየተጋ መሆኑን የፓርቲው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። ፓርቲው "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ ማኒፌስቶውንና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱን በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ለአባላቱና ለደጋፊዎቹ አስተዋውቋል። የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው፣ ፓርቲው ከተማዋን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ በኮሪደር ልማት፣ በስማርት ሲቲና በአረንጓዴ ልማት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል።   አካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት በመገንባት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እየተጋ ያለ ፓርቲ መሆኑንም አንስተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞላ ሁሴን በበኩላቸው፣ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ልማትን በመስራት ለዘንድሮው ምርጫ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው ምርጫውን ለማሸነፍና የከተማዋን ዕድገት ለማፋጠን በተሻሉ ሀሳቦች ጠንክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ አባላትና ደጋፊዎች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን በትጋት እንዲሰሩ ጠይቀዋል።   የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፤ ፓርቲው ከተሞችን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የጀመራቸው ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት ማሳየታቸውን ገልጸዋል። ለዘመናት ተረስቶ የነበረውን የፋሲል ግንብ ቅርስ በማደስ ከተማዋን የቱሪስት መዳረሻ ማድረጉን ለአብነት በማንሳት።   በፓርቲው የጎንደር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተስፋ መኮንን በበኩላቸው፣ ፓርቲው ያልተማከለና አካታች ሥርዓት ለመገንባት እየተጋ መሆኑን ገልጸው አባላት ለስኬቱ እንዲተጉ ጠይቀዋል። በፓርቲው የምዕራብ ጎንደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ እንዳለው ማሩ፣ ፓርቲው የከተማና የገጠር ትስስርን በማጠናከር የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ መልካሙ ሽባባው፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፓርቲው በቁርጠኝነት እየሰራ ነው ብለዋል። ፓርቲው በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ የገባውን ቃል በተግባር ማሳካቱ ለዚህ ማሳያ ነው ብለዋል። በከተሞቹ በተካሄደው የማስተዋወቂያ መድረክ ላይ የፓርቲው ከፍተኛ ሃላፊዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች የተገኙ ሲሆን የፓርቲው የመወዳደሪያ ምልክት የስንዴ ነዶ መሆኑንም አስተዋውቋል።    
ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የትብብር አድማስ ለማስፋት ትሻለች - አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ
Feb 26, 2026 67
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር በታሪክ እና ባህል ያላትን ትስስር በሌሎች መስኮችም የማስፋት ፍላጎት እንዳላት በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ ገለጹ። አምባሳደር ዮሶን ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ጊዜ የቆየ ትስስር እንዳላቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። የአድዋ ድል በኮሎምቢያ ለሚኖሩ የአፍሮ-ካሪቢያን ዝርያ ላላቸው ዜጎች የክብር እና የተነሳሽነት ምንጭ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በአድዋ ድል የሰብዓዊነት እናት፣ የታጋይነት እና አይበገሬነት ምልክት ሆናለች ሲሉም ነው የተናገሩት። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለተካሄዱ የፀረ-ቅኝ ግዛት እንቅስቃሴዎች ቁልፍ ሚና አላት ብለዋል። የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው የኮሎምቢያ ዜጎች ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸው ትስስር ለሀገራቱ የባህል ትብብር የጠለቀ እንዲሆን አድርጎታልም ነው ያሉት አምባሳደሩ። አምባሳደር ዬሰን የኮሎምቢያ እና ኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እያደገ መምጣቱን አንስተው በተለይም ሀገራቱ በቡና ዘርፍ የቴክኒክ ልውውጦች እና የጋራ ውይይቶችን በቋሚነት እያደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ በቡና ምርት ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ ለመከላከል ሀገራቱ በትብብር እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል። ቡና ለሁለቱም ሀገራት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ዘርፍ መሆኑን ጠቁመው ለዜጎች የኑሮ መሻሻል እና የገቢ እድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል። በሌላ በኩል አምባሳደሩ የአዲስ አበባን ፈጣን ለውጥ በማድነቅ ከኮሎምቢያ መዲና ቦጎታ ጋር ያላትን ትብብር አንስተዋል። ቦጎታ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የከተማ ሪፎርሞች ውስጥ ማለፏን አውስተው ሁለቱ ከተሞች ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የከተማ ልማትን ለማስፋት የልምድ ልውውጦችን እያደረጉ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗንም ጨምረው አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ እና ኮሎምቢያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ 1947 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ኮሎምቢያ በነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኤምባሲ ዳግም መክፈቷ የሚታወስ ሲሆን ይህም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ብልጽግና በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን አስመዝግቧል 
Feb 26, 2026 72
ደሴ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገቡ ተገለጸ። በአጭር ጊዜ ውስጥ የተከናወኑ የልማት ተግባራት የኢትዮጵያን ብልጽግና አይቀሬነት ያሳያሉ ፓርቲው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመወዳደሪያ ምልክቱንና ማኒፌስቶውን በደሴ፣ ወልዲያና ደብረ ብርሃን ከተሞች ለደጋፊዎችና ለአባላቱ ዛሬ አስተዋውቋል። የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን ፣ በፓርቲው የሚመራው መንግስት ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በመገንባት በማዕድን፣ በቱሪዝምና በሌሎች ዘርፎች አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋ ዳኛው በበኩላቸው፣ ብልጽግና በመደመር ፍልስፍና የወል ትርክትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ላይ የተመሰረተች ሀገር ለመገንባት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደሴ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁ ፣ ፓርቲው ኢትዮጵያን ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና በማሸጋገር ላይ መሆኑን ለአባላትና ደጋፊዎች ገልጸዋል። በተመሳሳይ በብልጽግና ፓርቲ የወልዲያ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ገብሬ በማስተዋወቂያ ፕሮግራሙ ላይ ፓርቲው ለችግሮች ሳይበገር በርካታ ውጤቶችን ያስመዘገበ ነው ብለዋል። በፓርቲው የሚመራው መንግስት በኢትዮጵያ ታሪክ ያልተሞከሩ በርካታ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን በማድረግ የሀገሪቱ ከፍታና የህዝቡ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   በዚህም ባለፉት ዓመታት ሀገሪቱ ከፍ ብላ የምትታይባቸውን የህዳሴ ግድብን በማጠናቀቅ እንዲሁም በርካታ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመገንባት ውጤት ማስመዝገቡን ጠቅሰዋል። በበጋ ስንዴና ሌማት ትሩፋት ጨምሮ በሌሎችም የልማት መስኮች ለውጥ ማምጣቱን አመልክተዋል ። ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን የምግብ ሉአላዊነትን በማረጋገጥ ከተረጅነት የተላቀቀች ሀገር ለመፍጠር እየሰራ ያለው ስራ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲው የተጀመሩ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ፈጥኖ በማጠናቀቅ ለህዝብ ተጠቃሚነት እየሰራ ይገኛል። ሌሎች የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችንም በማጠናቀቅ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምእራፍ ለማሸጋገር እየተጋ መሆኑን አስታውቀዋል።
በአጭር ጊዜ ውስጥ የተከናወኑ የልማት ተግባራት የኢትዮጵያን ብልጽግና አይቀሬነት ያሳያሉ
Feb 26, 2026 104
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- በብልጽግና ፓርቲ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያ ብልጽግናን አይቀሬነት እንደሚያሳዩ ተመላከተ። የወላይታ ዞንና የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር በጋራ በመሆን "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ ምልክት (የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሄደዋል። ብልፅግና ፓርቲ በጥቂት ዓመታት በሁሉም ዘርፍ ከፍተኛ ዕድገትና ስኬት ያስመዘገበ ፓርቲ ነው -ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) በወቅቱም የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ እንደገለፁት፤ ብልጽግና ፓርቲ ሥር የሰደዱ ስብራቶችን ለመጠገን የወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች ስኬት የተመዘገበባቸው ናቸው።   ለአብነትም ማሕበረሰቡ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እንዲሸጋገር ተጨባጭ ሥራዎች የተሰሩ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በተካሔደው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴን አምርቶ ወደ ውጭ መላክ መጀመሩንም ነው የጠቀሱት። የስንዴ ነዶ የመደመር እሳቤያችን ተምሳሌት በመሆኑ አቅማችንን አሰባስበንና ጉልበታችንን አስተባብረን በአጭር ጊዜ ውስጥ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እንሠራለን ሲሉም ተናግረዋል። እስካሁን የተከናወኑ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬ ለመሆኑ ማሳያዎች ናቸው ብለዋል።   ፓርቲው የዜጎችን እና የሀገርን ክብር የሚያስጠብቅ የዲፕሎማሲ አካሄድን በመከተል ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ እንድትታይ ያደረገ መሆኑንም አብራርተዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማርያም በበኩላቸው፤ ብልጽግና የለውጥ ፍላጎቶችን መነሻ አድርጎ የተነሳ ሀገራችንን ከብተና ያዳነ ፓርቲ ነው ብለዋል።   በፓርቲው ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት ከተሞች እየዘመኑ እና እየተለወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በፓርቲው መሪነት የተካሔዱ የህዳሴ ግድብ ግንባታ፣ የስንዴ ልማት፣ የሌማት ትሩፋት እና ሌሎችም ዘርፎች የህዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ካሉ በርካታ ተግባራት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የስንዴ ነዶ የመደመር፣ የአንድነትና የትብብር ምልክት ከመሆን ባሻገር ፓርቲያችን የነደፈውን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የመሸጋገር ውጥን በማሳካት ከልመና የመውጣታችንም ምልክት ነው ብለዋል። በመሆኑም እንደ ነዶ እጅ ለእጅ ተያይዘን በመሥራት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከልመና የመውጣት ትልምን ለማሳካት መረባረብ አለብን ሲሉም ተናግረዋል።
ፖለቲካ
በሁሉም የልማት መስኮች የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን ያፋጠኑ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Feb 26, 2026 34
ቦንጋ/ሚዛን፤የካቲት19/2018 (ኢዜአ)፡-ብልጽግና ፓርቲ በሁሉም የልማት መስኮች የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ስኬቶችን በተግባር ማስመዝገቡ ተገለጸ። ፓርቲው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን የስንዴ ነዶ እና ማኒፌስቶውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሚዛን አማን እና ቦንጋ ከተሞች ዛሬ ለህዝብና ለደጋፊዎቹ አስተዋውቋል። በቦንጋ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ፣ ብልጽግና ባለፉት ዓመታት እዳን ወደ ምንዳ በመቀየር በፈጠራና በፍጥነት እሳቤ ሀገራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ እየተጋ ያለ ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው የተከተለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕሳቤ ኢትዮጵያ ከምትታወቅበት ድህነት ወጥታት በልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ለመሸጋገር የሚያስችላት መሆኑን ጠቅሰዋል። በፓርቲው መሪነት ባለፉት ዓመታት በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በቴክኖሎጂና በኢንዱስትሪ ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስኬቶች መመዝገባቸውንና ይህም ተጠናከሮ መቀጠሉን ነው የተናገሩት። በማህበራዊ ዘርፍም ሰው ተኮር የልማት ሥራዎችን በማከናወን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ ትችሏል ብለዋል። በዞኑ ሰፊ የልማት ሀብት ቢኖርም ትኩረት ባለመሰጠቱ ህዝቡ ተጠቃሚ ሳይሆን ቆይቷል ያሉት አስተዳዳሪው፣ በፓርቲው መሪነት በዞኑ ልማትን ለማፋጠን በተሰራው ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል። የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነው የስንዴ ነዶ የአብሮነት፣ የጥንካሬ፣ የአንድነትና በምግብ ራስን የመቻል መሆኑን ጠቁመው፣ ፓርቲውን መምረጥ ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ማስቀጠል ነው ብለዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የካፋ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ ሀይሌ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ብልፅግና ፓርቲ እንደሀገር የገጠሙ ስብራቶችን በመጠገንና ልማትን በማስቀጠል ዜጎችን ተጠቀሚ እያደረገ ይገኛል። በካፋ ዞን ሁለንተናዊ ለውጥ ለማስመዝገብ በትኩረት በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት እየመጣ ነው ያሉት ሀላፊው፣ በዚህም የዞኑ ነዋሪዎች ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መጥቷል ብለዋል። ዞኑ በልማት ወደኋላ ቀርቶ እንደነበረ አቶ አጥናፉ አስታውሰው፣ በፓርቲው መሪነት ይህን ለመቀየር የተወሰደ እርምጃ ህዝብን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።   በተመሳሳይ ዜና በሚዛን አማን ከተማ በተከሄደ መድረክ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን እንዳሉት ፓርቲው የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ሥራዎችን በተጨባጭ እያከናወነ ይገኛል። ምርጫ ለአንድ ሀገር ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ በመሆኑ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።   በፓርቲው መሪነት ባለፉት የለውጥ ዓመታት በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችና አዳዲስ እሳቤዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ የልማት ተምሳሌት የሚያደርጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። "ብልጽግና የሕዝብ ተጠቃሚነትን ያረጋገጡና ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ሥራዎችን በተጨባጭ ያስመዘገበና ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን ዓልሞ የሚሰራ ነው" ሲሉ አክለዋል። ዞኑ ከሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት ተጠቃሚ መሆኑን የገለጹት አስተዳዳሪው፣ በብዝሃ ኢኮኖሚ እይታ የተገነባው የደንቢ ኢኮ ሎጅ ለዚህ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል ፓርቲው ድህነትን ለማሸነፍ በግብርና ዘርፍ የጀመራቸው ኢኒሼቲቮች ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበባቸው በመሆኑ የማኅበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ነው ብለዋል። ብልጽግና የኢኮኖሚ አማራጭ መፍጠሩ በአካባቢያችን ያሉ አንጡራ ሀብቶችን አውጥቶ ለመጠቀም አስችሏል ያሉት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የቤንች ሸኮ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኩድን ናቸው። በቦንጋና በሚዛን አማን ከተማ በተካሄዱ መድረኮች የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የህብረተሰብ ተወካዮች፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።      
ኢትዮጵያ የገነባችው አስተማማኝ ሠራዊት በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና ነው
Feb 26, 2026 46
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የገነባችው አስተማማኝ ሠራዊት በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና መሆኑን የቀድሞው የአየር ወለድ አዛዥና ወደር የሌለው የኢትዮጵያ የጦር ሜዳ ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ገለጹ፡፡ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በተከበረበት ወቅት፣ ከኢትዮጵያ ባለፈ የቀጣናውንና የአፍሪካን ነጻነትና ሰላም ዛሬም እንደትናንቱ የሚያስከብር አስተማማኝ ኤሊት ፎርስ ተገንብቷል ብለዋል፡፡ የሠራዊቱ የተሟላ ዝግጁነት በድፍን አፍሪካ ሰላም እና ብልጽግናን ለማረጋገጥ በቀጣናው ላሉ ሀገራትም አለኝታና መከታ እንደሚሆን ገልጸዋል። የቀድሞው የአየር ወለድ አዛዥና ወደር የሌለው የኢትዮጵያ የጦር ሜዳ ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ወታደራዊ ሳይንስን፣ ስነ-ልቦናዊ ግንባታን እና የአካል ብቃትን መሠረት አድርጎ የተገነባ ሠራዊት ለሀገር ህልውና ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ስልጠና የድል በር መክፈቻ ቁልፍ ነው ያሉት ብርጋዴር ጀነራሉ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለችው ሠራዊት ጥራት ያለው፣ በሁሉም መልኩ የተዘጋጀ አስተማማኝ ኃይል መሆኑን ገልጸዋል።   በ65ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የምስረታ በዓል የተመለከቱት የሠራዊቱ ትርኢትም በሁኔታዎች የማይበገር ወሳኝ ኃይል መገንባቱን ያሳየ ነው ብለዋል። "በሕይወት ኖሬ የኢትዮጵያ ሠራዊት በዚህ መልኩ ተገንብቶ በማየቴ እንደገና እንደተወለድኩ ነው የቆጠርኩት" ሲሉም ነው የገለጹት። ኢትዮጵያ አሁን ላይ የገነባችው ኃይል የራሷን ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ ባለፈ የአካባቢው ሀገራት ጭምር የሚታመኑበትና ዋስትና የሚሆናቸው ኃይል ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን ሠራዊት ቁመና እና ጥንካሬ ያደነቁት ብርጋዴር ጀኔራሉ፥ ይህም ሀገራችን በቀጣናው ያላትን የሠላም አለኝታነት የሚያጸና መሆኑን ገልጸዋል። ሠራዊቱ ሁሉንም አቀፍ እውቀትና ዘመናዊ ትጥቅ የታጠቀ በመሆኑ በአየር፣ በባህር፣ በየብስ እንዲሁም በየትኛውም አውድና የመሬት ገፅ ድል አብሳሪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ብርጋዴር ጀኔራል ተስፋዬ አክለውም ኢትየጵያ ተግባርና ኃላፊነቱን ጠንቅቆ የሚያውቅ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸና ከራሷ አልፎ ለአፍሪካውያን ሠላም ዋስትና የሚሆን ሠራዊት መገንባቷን አመልክተዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምጽዋ ጫፍ በባህር ላይ የሚያጋጥሙ ሽብሮችን የሚያስቀር ኤሊት ፎርስ መገንባቱን መግለጻቸው ይታወቃል። ተቋም የምንገነባው፣ ኤሊት ፎርስ የምንገነባው፤ በቀጣናችን ውጊያና ሽብር እንዳይፈጠር ነው፤ ሲፈጠርም በአጠረ ጊዜ ለመቋጨት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ይህን አይነት ተቋም በመገንባቷ የምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ሀገራት እንኳን ደስ አላችሁ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በለውጡ መንግስት የተመዘገቡ የልማት ውጤቶች የጌዴኦ ዞን ህዝብን ተጠቃሚ አድርገዋል
Feb 26, 2026 83
ዲላ፣ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡-በጌዴኦ ዞን ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ የተመዘገቡ የልማት ውጤቶች የህዝቡን ተጠቃሚነት በተጨባጥ ያረጋገጡ መሆናቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። ብልጽግና ፓርቲ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ ማኒፌስቶውንና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን የስንዴ ነዶ በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ ለህዝብና ለፓርቲው ደጋፊዎች አስተዋውቋል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት ፓርቲው ሃገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርምን ተግባራዊ በማድረግ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋጋር ተግቶ እየሰራ ነው። በዚህም የጌዴኦ ህዝብ በተለያዩ የልማት ዘርፎች ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ በተለይ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ውጤት አመርቂ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ በቡና ልማት በሄክታር እስከ 19 ኩንታል በማግኝት ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበው ቡና ከ40 ሺህ ቶን በላይ መድረሱን በማሳያነት ጠቅሰዋል። በእንሰትና ፍራፍሬ ልማትም የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻሉን አንስተው ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በፓርቲው መሪነት በዞኑ የመጡ ድሎችን ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የዞኑ ህዝብም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ምርጫው ስላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል።   በከተማው ባለፉት አምስት ዓመታት የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ጨምሮ ከ252 በላይ የልማት ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት በማብቃት ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ መሰጠቱን ያነሱት ደግሞ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ናቸው። በተለይ በከተማው ሁሉንም የመንግስት አገልግሎት በማዘመንና ዲጂታል በማድረግ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ተችሏል ብለዋል። በዚህም የህዝብን የዘመናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት በተሰራው ስራ ውጤት መመዝገቡን ነው ያስታወቁት። ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብን ይሁንታ ካገኘ እነዚህን የተመዘገቡ ውጤቶች በማጠናከር ለላቀ የህብረተሰብ ተጠቃሚነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። ‎በብልጽግና ፓርቲ የጌዴኦ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፍት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር ተመስገን ጥላሁን በበኩላቸው ‎ጠቅላላ ምርጫው የፓርቲው የመወዳደሪያ ምልክት የስንዴ ነዶ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻልና የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ በገጠርና በከተማ በተለያዩ መስኮች እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። ‎ በመርሐ ግብሩ ላይ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ወጣቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና በርካታ የፓርቲው ደጋፊዎች ተገኝተዋል።    
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል
Feb 26, 2026 84
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለኢትዮጵያ ዕድገትና ለህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን በሸገር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ። የዘንድሮው ኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ማሳወቁ ይታወቃል። በዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትና ማኒፌስቷቸውን በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። ዜጎችም በመጪው ግንቦት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚችሉበትን ካርድ ለመውሰድ እየተጠባበቁ ይገኛል። የሸገር ከተማ ነዋሪ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለኢዜአ እንዳሉትም፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለህዝብና ለሀገር ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት በማፋጠን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅምና አንድነት ለሚሰራ የፓለቲካ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት በምርጫ ሂደቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ነጋሽ ኢደኦ እንዳሉት፤ ምርጫ ዜጎች ለሀገርና ህዝብ አንድነት ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ የሚመርጡበት ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫም የሀገርን ዕድገት፣ የህዝብን አንድነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትጋት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።   ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ሀዳ ሲንቄ ጫልቱ ቀነዓ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምርጫ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማፋጠን ለሀገር ዕድገት የሚረዳ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣዩ ጠቅላላ ምርጫም የኢትዮጵያን ሰላም፣ ልማትና ዕድገት በማሳለጥ ለዜጎች አንድነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ምርጫ የአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መገለጫ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ድጋፌ ኤዪ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው።   በዚህም በቀጣዩ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቦች ሕብረብሔራዊ አንድነትና ተጠቃሚነት እንዲሁም ለሀገር ዕድገት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል። ዜጎችም ሀገርን በሚገባ በማስተዳደር ዕድገትና ልማትን ያፋጥናል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ምርጫው ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሕዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የማድረግ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።   የሸገር ከተማ ነዋሪ ወጣት ኢፌ ባልቻ በበኩሏ፤ በጠቅላላ ምርጫው ላይ ለሀገርና ህዝብ ይበጃል የምለውን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ ድምጽ ለመስጠት ጊዜውን እየተጠባበኩ ነው ብላለች። በተለይም የኢትዮጵያና የሸገር ከተማን ልማት በማፋጠን የህዝቦች አንድነት፣ የሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ እንደምትሰጥ ገልፃለች። ወጣቶችም በመጪው ግንቦት ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማነት የሚጠበቅባቸውን ገንቢ ኃላፊነት መወጣት እንደሚኖርባቸው ጠቅሳለች።      
ብልጽግና ፓርቲ አካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት በመገንባት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ ይተጋል -የፓርቲው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች
Feb 26, 2026 87
ባህርዳር/ጎንደር/ገንዳ ውሃ/ደብረ ማርቆስ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ አካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት በመገንባት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እየተጋ መሆኑን የፓርቲው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። ፓርቲው "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሀሳብ ማኒፌስቶውንና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱን በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ለአባላቱና ለደጋፊዎቹ አስተዋውቋል። የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው፣ ፓርቲው ከተማዋን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ በኮሪደር ልማት፣ በስማርት ሲቲና በአረንጓዴ ልማት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል።   አካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት በመገንባት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እየተጋ ያለ ፓርቲ መሆኑንም አንስተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞላ ሁሴን በበኩላቸው፣ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ልማትን በመስራት ለዘንድሮው ምርጫ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው ምርጫውን ለማሸነፍና የከተማዋን ዕድገት ለማፋጠን በተሻሉ ሀሳቦች ጠንክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ አባላትና ደጋፊዎች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን በትጋት እንዲሰሩ ጠይቀዋል።   የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፤ ፓርቲው ከተሞችን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የጀመራቸው ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት ማሳየታቸውን ገልጸዋል። ለዘመናት ተረስቶ የነበረውን የፋሲል ግንብ ቅርስ በማደስ ከተማዋን የቱሪስት መዳረሻ ማድረጉን ለአብነት በማንሳት።   በፓርቲው የጎንደር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተስፋ መኮንን በበኩላቸው፣ ፓርቲው ያልተማከለና አካታች ሥርዓት ለመገንባት እየተጋ መሆኑን ገልጸው አባላት ለስኬቱ እንዲተጉ ጠይቀዋል። በፓርቲው የምዕራብ ጎንደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ እንዳለው ማሩ፣ ፓርቲው የከተማና የገጠር ትስስርን በማጠናከር የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ መልካሙ ሽባባው፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፓርቲው በቁርጠኝነት እየሰራ ነው ብለዋል። ፓርቲው በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ የገባውን ቃል በተግባር ማሳካቱ ለዚህ ማሳያ ነው ብለዋል። በከተሞቹ በተካሄደው የማስተዋወቂያ መድረክ ላይ የፓርቲው ከፍተኛ ሃላፊዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች የተገኙ ሲሆን የፓርቲው የመወዳደሪያ ምልክት የስንዴ ነዶ መሆኑንም አስተዋውቋል።    
ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የትብብር አድማስ ለማስፋት ትሻለች - አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ
Feb 26, 2026 67
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር በታሪክ እና ባህል ያላትን ትስስር በሌሎች መስኮችም የማስፋት ፍላጎት እንዳላት በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ ገለጹ። አምባሳደር ዮሶን ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ጊዜ የቆየ ትስስር እንዳላቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። የአድዋ ድል በኮሎምቢያ ለሚኖሩ የአፍሮ-ካሪቢያን ዝርያ ላላቸው ዜጎች የክብር እና የተነሳሽነት ምንጭ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በአድዋ ድል የሰብዓዊነት እናት፣ የታጋይነት እና አይበገሬነት ምልክት ሆናለች ሲሉም ነው የተናገሩት። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለተካሄዱ የፀረ-ቅኝ ግዛት እንቅስቃሴዎች ቁልፍ ሚና አላት ብለዋል። የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው የኮሎምቢያ ዜጎች ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸው ትስስር ለሀገራቱ የባህል ትብብር የጠለቀ እንዲሆን አድርጎታልም ነው ያሉት አምባሳደሩ። አምባሳደር ዬሰን የኮሎምቢያ እና ኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እያደገ መምጣቱን አንስተው በተለይም ሀገራቱ በቡና ዘርፍ የቴክኒክ ልውውጦች እና የጋራ ውይይቶችን በቋሚነት እያደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ በቡና ምርት ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ ለመከላከል ሀገራቱ በትብብር እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል። ቡና ለሁለቱም ሀገራት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ዘርፍ መሆኑን ጠቁመው ለዜጎች የኑሮ መሻሻል እና የገቢ እድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል። በሌላ በኩል አምባሳደሩ የአዲስ አበባን ፈጣን ለውጥ በማድነቅ ከኮሎምቢያ መዲና ቦጎታ ጋር ያላትን ትብብር አንስተዋል። ቦጎታ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የከተማ ሪፎርሞች ውስጥ ማለፏን አውስተው ሁለቱ ከተሞች ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የከተማ ልማትን ለማስፋት የልምድ ልውውጦችን እያደረጉ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗንም ጨምረው አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ እና ኮሎምቢያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ 1947 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ኮሎምቢያ በነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኤምባሲ ዳግም መክፈቷ የሚታወስ ሲሆን ይህም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ብልጽግና በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን አስመዝግቧል 
Feb 26, 2026 72
ደሴ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገቡ ተገለጸ። በአጭር ጊዜ ውስጥ የተከናወኑ የልማት ተግባራት የኢትዮጵያን ብልጽግና አይቀሬነት ያሳያሉ ፓርቲው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመወዳደሪያ ምልክቱንና ማኒፌስቶውን በደሴ፣ ወልዲያና ደብረ ብርሃን ከተሞች ለደጋፊዎችና ለአባላቱ ዛሬ አስተዋውቋል። የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን ፣ በፓርቲው የሚመራው መንግስት ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በመገንባት በማዕድን፣ በቱሪዝምና በሌሎች ዘርፎች አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋ ዳኛው በበኩላቸው፣ ብልጽግና በመደመር ፍልስፍና የወል ትርክትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ላይ የተመሰረተች ሀገር ለመገንባት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደሴ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁ ፣ ፓርቲው ኢትዮጵያን ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና በማሸጋገር ላይ መሆኑን ለአባላትና ደጋፊዎች ገልጸዋል። በተመሳሳይ በብልጽግና ፓርቲ የወልዲያ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ገብሬ በማስተዋወቂያ ፕሮግራሙ ላይ ፓርቲው ለችግሮች ሳይበገር በርካታ ውጤቶችን ያስመዘገበ ነው ብለዋል። በፓርቲው የሚመራው መንግስት በኢትዮጵያ ታሪክ ያልተሞከሩ በርካታ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን በማድረግ የሀገሪቱ ከፍታና የህዝቡ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   በዚህም ባለፉት ዓመታት ሀገሪቱ ከፍ ብላ የምትታይባቸውን የህዳሴ ግድብን በማጠናቀቅ እንዲሁም በርካታ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመገንባት ውጤት ማስመዝገቡን ጠቅሰዋል። በበጋ ስንዴና ሌማት ትሩፋት ጨምሮ በሌሎችም የልማት መስኮች ለውጥ ማምጣቱን አመልክተዋል ። ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን የምግብ ሉአላዊነትን በማረጋገጥ ከተረጅነት የተላቀቀች ሀገር ለመፍጠር እየሰራ ያለው ስራ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲው የተጀመሩ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ፈጥኖ በማጠናቀቅ ለህዝብ ተጠቃሚነት እየሰራ ይገኛል። ሌሎች የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችንም በማጠናቀቅ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምእራፍ ለማሸጋገር እየተጋ መሆኑን አስታውቀዋል።
በአጭር ጊዜ ውስጥ የተከናወኑ የልማት ተግባራት የኢትዮጵያን ብልጽግና አይቀሬነት ያሳያሉ
Feb 26, 2026 104
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- በብልጽግና ፓርቲ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያ ብልጽግናን አይቀሬነት እንደሚያሳዩ ተመላከተ። የወላይታ ዞንና የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር በጋራ በመሆን "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ ምልክት (የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሄደዋል። ብልፅግና ፓርቲ በጥቂት ዓመታት በሁሉም ዘርፍ ከፍተኛ ዕድገትና ስኬት ያስመዘገበ ፓርቲ ነው -ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) በወቅቱም የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ እንደገለፁት፤ ብልጽግና ፓርቲ ሥር የሰደዱ ስብራቶችን ለመጠገን የወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች ስኬት የተመዘገበባቸው ናቸው።   ለአብነትም ማሕበረሰቡ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እንዲሸጋገር ተጨባጭ ሥራዎች የተሰሩ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በተካሔደው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴን አምርቶ ወደ ውጭ መላክ መጀመሩንም ነው የጠቀሱት። የስንዴ ነዶ የመደመር እሳቤያችን ተምሳሌት በመሆኑ አቅማችንን አሰባስበንና ጉልበታችንን አስተባብረን በአጭር ጊዜ ውስጥ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እንሠራለን ሲሉም ተናግረዋል። እስካሁን የተከናወኑ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬ ለመሆኑ ማሳያዎች ናቸው ብለዋል።   ፓርቲው የዜጎችን እና የሀገርን ክብር የሚያስጠብቅ የዲፕሎማሲ አካሄድን በመከተል ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ እንድትታይ ያደረገ መሆኑንም አብራርተዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማርያም በበኩላቸው፤ ብልጽግና የለውጥ ፍላጎቶችን መነሻ አድርጎ የተነሳ ሀገራችንን ከብተና ያዳነ ፓርቲ ነው ብለዋል።   በፓርቲው ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት ከተሞች እየዘመኑ እና እየተለወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በፓርቲው መሪነት የተካሔዱ የህዳሴ ግድብ ግንባታ፣ የስንዴ ልማት፣ የሌማት ትሩፋት እና ሌሎችም ዘርፎች የህዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ካሉ በርካታ ተግባራት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የስንዴ ነዶ የመደመር፣ የአንድነትና የትብብር ምልክት ከመሆን ባሻገር ፓርቲያችን የነደፈውን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የመሸጋገር ውጥን በማሳካት ከልመና የመውጣታችንም ምልክት ነው ብለዋል። በመሆኑም እንደ ነዶ እጅ ለእጅ ተያይዘን በመሥራት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከልመና የመውጣት ትልምን ለማሳካት መረባረብ አለብን ሲሉም ተናግረዋል።
ማህበራዊ
ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከአጋር አካላት ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ ነው
Feb 26, 2026 43
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከአጋር አካላት ጋር የተቀናጀ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በካንሰር ምርምር ላይ የሚያተኩረውን የelse korner center fore cancer care (EKC 2) ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍን በመጠናቀቅ ሁለተኛውን ምዕራፍ ይፋ አድርጓል፡፡   ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት ለቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚተገበር ሲሆን የሴቶችን የካንሰር ሕክምና አገልግሎት በየአካባቢው ተደራሽ ማድረግ፣ ስለ ጡት እና ማህፀን በር ካንሰር ግንዛቤን ማሳደግ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሕይወት ሰለሞን በዚሁ ወቅት፤ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ከመከሰታቸው በፊት በቅድመ ጥንቃቄ መከላከል ይቻላል ብለዋል፡፡ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በሰዎች ላይ የሚያስከትሉትን ማኅበራዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ለመግታት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል፡፡ መንግስት የበሽታዎቹን ስርጭት ለመግታት ከግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ባሻገር ሌሎች ውጤታማ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ህብረተሰቡ የሚያደርገውን ጥንቃቄ ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የካንሰርና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርምር ክፍል አስተባባሪ ዶክተር አዳሙ አዲሴ በበኩላቸው፤ የካንሰር በሽታ በአፍሪካ ደረጃ አሳሳቢነቱ እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመዋል። ይህንን ለመቅረፍ ኮሌጁ ችግር ፈቺ በሆኑ ምርምሮች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑንና የኤልሳ ክሮነር የካንሰር ሕክምና ማዕከል ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ገልጸዋል።   የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ የጤና ማጎልበትና በሽታ መከላከል ዳይሬክተር አቶ ጌቱ ቢሳ እንደገለጹት፣ ፕሮጀክቱ በተለይ በእናቶች ላይ የሚከሰቱ የጡትና የማህፀን በር ካንሰር ለመቀነስ ትልቅ ሚና አለው። ቀደም ሲል በተመረጡ ሆስፒታሎች ብቻ ይሰጥ የነበረው አገልግሎት አሁን በፕሮጀክቱ አማካኝነት ወደ ጤና ጣቢያዎች ዝቅ እንዲል መደረጉንም ጠቅሰዋል፡፡
በድሬደዋ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ተደራሽነትና አገልግሎቶች ይጠናከራሉ - ከንቲባ ከድር ጁሃር
Feb 26, 2026 77
ድሬደዋ፣ የካቲት 19/2018(ኢዜአ):- በድሬደዋ ለተገልጋዩ ፈጣንና ተደራሽ የፍርድ አገልግሎት በመስጠት ወሳኝ ሚና እያበረከቱ የሚገኙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ይጠናከራሉ ሲሉ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። በድሬደዋ አስተደዳር የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ምክርቤት የማቋቋምና ለባህላዊ ፍርድ ቤቶች ዕውቅና የመስጠት ስነስርአት ዛሬ በይፋ ተካሂዷል።   በስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር በወቅቱ እንዳሉት፤ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ለዜጎች ተደራሽ አገልግሎት በመስጠት የመደበኛ ፍርድ ቤቶችን ጫና እያቃለሉ ናቸው። የፍትህ አገልግሎቱ እንዲሻሻል እያከናወኑ ያሉትን አበረታች ተግባራት ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚመሩበት የህግ ማዕቀፍ በአስተዳደሩ ምክርቤት ፀድቆ ወደ ስራ መገባቱንም አስታውሰዋል። በመሆኑም ባህላዊ ፍርድ ቤቶቹ ውጤታማ ስራ እንዲያከናውኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው የምክርቤቱ መቋቋም ወሳኝ እርምጃ ነው ብለዋል ።   የድሬደዋ አስተዳደር ፍትህ፣ ፀጥታና የህግ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱሰላም አህመድ በበኩላቸው የባህላዊ ፍርድ ቤቶች የሚከተሉት የአሰራር ስነስርአት ማህበረሰቡን ተደራሽ በማድረግ የፍትህ አገልግሎት እንዲያገኝና ማህበራዊ መስተጋብር እንዲጠናከር እያስቻሉ መሆኑን አንስተዋል። ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚለያቸውን ድንበርና አሰራር በመለየት የሚፈለገውን ውጤታማ ስራ እንዲያከናውኑ አስፈላጊው ድጋፍና እገዛ እንደሚደረግላቸው በማስታወቅ። የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ባህላዊ ህጎችና እሴቶችን በመጠበቅና የማህበረሰቡን መስተጋብር በማጠናከር የመደበኛ ፍርድ ቤቶችን የስራ ጫና እያቃለሉ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የድሬደዋ አስተዳደር የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች ፕሬዚዳንት አቶ ነጂብ ኢድሪስ ናቸው።   በተጨማሪም የሃብትና የጊዜ ብክነትን በመከላከል ምርታማነት ይበልጥ እንዲጎለብት አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ የተሰጣቸው ዕውቅና በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት እንደሚያስችላቸው ነው አቶ ነጂብ የተናገሩት።   የኃይማኖት አባቶችና ታዋቂ የአገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎችና ኡጋዞች፣ በየደረጃው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የተመሰረተው የባህላዊ ፍርድ ቤት ምክርቤት አባላት መሆናቸውን በስነስርዓቱ ላይ ተመልክቷል።
ለብሔራዊ ጥቅም መቆም ለዘመናት የቆየ የአብሮነትና የሀገር ፍቅር ውጤት ነው
Feb 26, 2026 62
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ለብሔራዊ ጥቅም መቆም ለዘመናት የዳበረ የአብሮነትና የሀገር ፍቅር ውጤት ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። 130ኛ የአድዋ ድል በዓል አስመልክቶ፣ "ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።   በዚህ ወቅት ቢሮ ሀላፊዋ እንደተናገሩት የአድዋ ድል የሀገራችንን ዕጣ ፈንታ የሚቀይር፣ አንድነቷ የጸና እና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚያነሳሳ ነው። የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅም የዚሁ "ዳግማዊ አድዋ" ህያው ማሳያ እንደሆነና ለሌሎች ሁለንተናዊ ስኬቶች መነሳሳት እንደሚሆን ተናግረዋል። የዘንድሮው 130ኛው የአድዋ ድል በዓል በዋናነት በይቻላል መንፈስ ውጤቶቻችንን እና መልካም ገጽታችንን ለዓለም ያሳየንበት፣ በንጋት ሃይቅና በጉባ ተራሮች ላይ የብልጽግና ብስራቶችን ያወጅንበት እና 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚከናወንበት ወቅት ላይ መሆናችን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።   በውይይቱ ላይ "የአድዋ አደራ አንድነት፣ ሉዓላዊነትና ማንሰራራት!" በሚል የመወያያ ሰነድ መቅረቡን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።   በመድረኩ የመከላከያ ሰራዊት የዘመቻ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል በላይ ስዩም፣ የአድዋ ድል በዓል የነጻነት ተምሳሌት በመሆኑ ትውልዱ ታሪኩን ጠብቆ ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ አለበት ብለዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ባስተላለፉት መልዕክት የህዳሴው ግድብ ዳግማዊ አድዋ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የጤና ጣቢያ ግንባታው የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት የሚደረግን የረጅም ርቀት ጉዞን አስቀርቷል - ነዋሪዎች
Feb 26, 2026 57
መተማ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- በቀበሌያቸው የጤና ጣቢያ ተገንብቶ ለአገልግሎት በመብቃቱ ወደ ሌሎች አካባቢዎች የሚያደርጉትን የጉዞ እንግልትና ወጪን እንዳስቀረላቸው በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የጤና ተቋማትን ደረጃ ማሻሻል ቁልፍ ተግባር ነው የጤና ጣቢያ ግንባታው ለሕክምና አገልግሎት ረጅም ርቀት መጓዝን ከማስቀረት ባለፈ ጊዜና ጉልበታቸውን ለልማት እንዲያውሉ እንዳገዛቸውም ነዋሪዎቹ አመልክተዋል። በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ የኩመር አፍጥጥ ቀበሌ ነዋሪዎች፣ በአቅራቢያቸው በተገነባው ጤና ጣቢያ ተገቢውን የሕክምና አገልግሎት ማግኘት መጀመራቸውን ገልጸዋል።   ቀደም ሲል ለሕክምና አገልግሎት ወደ ገንዳ ውኃ ከተማ ይሄዱ እንደነበር አስታውሰው፣ ይህም ለከፍተኛ ወጪና እንግልት ዳርጎናል ብለዋል። የቀበሌው ነዋሪ አየሁሽ ስመኘው እንደገለጹት፣ የጤና ጣቢያው በአቅራቢያቸው መገንባቱ ያለምንም እንግልት ፈጣን ሕክምና እንዲያገኙ ረድቷቸዋል። ቀደም ሲል ወደ ገንዳ ውኃ በመሄድ ይባክን የነበረ ጊዜና ገንዘብን በመቆጠብ ለልማት ሥራ ማዋል መቻላቸውን ተናግረዋል። ሌላዋ ነዋሪ ስፍራሽ ጌጡ የጤና ጣቢያው ግንባታ የእናቶችና ህጻናትን ጤና ከማሻሻል አኳያ ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። በጤና ጣቢያው የሕፃናት የተመጣጠነ ምግብ ዝግጅትን አስመልክቶ የሚሰጠው ትምህርት ለህጻናት ጤናና ለተሻለ ዕድገት ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።   የምዕራብ ጎንደር ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ጅብሪል መርሻ፣ በዞኑ ካሉት 23 የጤና ተቋማት መካከል ዘንድሮ ግንባታቸው ተጠናቆ ወደ ሥራ ከገቡት ሁለቱ ጤና ጣቢያዎች አንዱ የአፍጥጥ ጤና ጣቢያ መሆኑን ገልጸዋል። ጤና ጣቢያው ከሌሎች የሕክምና አገልግሎቶች በተጨማሪ ከ120 በላይ ለሚሆኑ የሥነ-አእምሮ ሕሙማን ተገቢው ሕክምና መስጠቱንም ገልጸዋል። ዞኑ ሰፊ የእርሻ ኢንቨስትመንት የሚካሄድበት እንደመሆኑ የነዋሪውንና የሠራተኛውን ጤና መጠበቅ ለምርታማነት ዕድገት ወሳኝ ነው ብለዋል።
ኢኮኖሚ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን በሚደረገው ጥረት አበረታች ውጤት ተገኝቷል
Feb 26, 2026 82
አሶሳ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን በሚደረገው ጥረት አበረታች ውጤት መገኘቱን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። በክልሉ የሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን በኮሚሽኑ አማካኝነት በአቡራሞ ወረዳ የለማ ሰብል ተሰብስቧል። የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሐመድ አብዱላዚዝ፣ እንዳሉት በ2016/17 የምርት ዘመን ለሰብዓዊ ድጋፍ ታስቦ በውስን አካባቢዎች የተጀመረው የሰብል ልማት አበረታች ውጤት ተገኝቶበታል።   በዘንድሮው ዓመት በክልሉ 1 ሺህ 804 ሄክታር ማሳ ላይ በለማው የበቆሎ፣ ማሽላ፣ አኩሪ አተር እና ሌሎች ሰብሎች እስከአሁን ድረስ 36 ሺህ 211 ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል። በምርት ዘመኑ ከ43 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፥ የምርት አሰባሰብ ሂደቱ ሲጠናቀቅ ዕቅዱ ሙሉ ለሙሉ እንደሚሳካ ጠቁመዋል። የክልሉ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን በራሱ አቅም በክልሉ አቡራሞ እና ሆሞሻ ወረዳዎች ላይ ካለማው ማሳ 2 ሺህ 200 በላይ ኩንታል ምርት መሰብሰቡንም ተናግረዋል። የተሰበሰበው ምርት የውጪ እርዳታን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚያግዝና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ጉልህ ድርሻ እንዳለውም ተናግረዋል። ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተያዘውን ሀገራዊ ግብ ለማሳካት መንግስት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ኮሚሽነሩ ምርቱም ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ይደረጋል ብለዋል። በቀጣይም በክልሉ የሚገኙ ሰፋፊ የእርሻ ማሳዎችን በማስፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እና ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን የዜሮ ፕርሰንት ሀገራዊ ግብ ለማሳካት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል ።  
በአማራ ክልል የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋንን የሚያሳድጉ የውሃ ተቋማት ግንባታ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Feb 26, 2026 80
ባህር ዳር ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋንን የሚያሳድጉ የውሃ ተቋማት ግንባታ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ገለጸ። በክልሉ በተከናወኑ የውሃ ተቋማት ግንባታና ጥገና ከ170 ሺህ በላይ ዜጎች የንጹሕ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሆነዋል። የውሃ ተቋማቱ በተለይም በገጠርና በከተማ የሚገኙ እናቶችንና ሕፃናትን ከእንግልት መታደግ ችለዋል። የአማራ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ጥላሁን ሽመልስ ለኢዜአ እንዳሉት በገጠርና ከተሞች የንፁህ መጠጥ ውሃ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ከ2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞ እየተከናወነ ነው። በተያዘው በጀት ዓመት ከሁለት ሺህ በላይ አነስተኛ የውሃ ተቋማትን ለመገንባት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አመልክተዋል። ባለፉት ሰባት ወራት ከሁለት ሺህ በላይ የውሃ ተቋማትን ወደ ግንባታ ማስገባት የተቻለ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ የ306ቱን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን አብራርተዋል። እንዲሁም የ55 ከፍተኛ የውሃ ተቋማት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከእነዚህ ውስጥ 17 የሚሆኑት ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ነው ያሉት። የውሃ ተቋማቱ ከ170 ሺህ በላይ ዜጎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን ገልጸው የክልሉን የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን እየተከናወኑ ያሉ ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ፣ በክልሉ ለብልሽት የተዳረጉ ከ13 ሺህ በላይ የውሃ ተቋማት በሕብረተሰብ ተሳትፎ ተጠግነው ለአገልግሎት በቅተዋል። የውሃ ተቋማቱን ዘላቂነት ለማረጋገጥም አደረጃጀት በመፍጠር የጥበቃና የእንክብካቤ ስራ እየተሰራ እንደሆነ አመልክተው በቀሪ ወራትም ግንባታቸው የተጀመሩ የውሃ ተቋማትን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እንዲበቁ በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምዕራብ በለሳ ወረዳ ነዋሪ ማሪቱ በላይነህ በአቅራቢያቸው የንፁህ መጠጥ ውሃ ባለመኖሩ ውሃ ፍለጋ ረጅም መንገድ በመጓዝ እንግልት ይደርስባቸው እንደነበር አስታውሰዋል። በአቅራቢያቸው ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው የውሃ ፕሮጀክት የቀደመ ችግራቸውን በመፍታቱ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆን እንደቻሉ ተናግረዋል። በዚህ ዓመት ተገንብቶ አገልግሎት የጀመረው የጋብላ ውሀ ፕሮጀክት የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግራችንን የፈታ ነው ያሉት ደግሞ በምዕራብ ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ጋብላ ከተማ ነዋሪ ግርማ ደግሰው ናቸው። ሌላኛዋ በዚሁ ወረዳ ጠረፍ ወርቅ ቀበሌ ነዋሪ ፋሲካ አንተነህ እንዳሉት፤ በፀሐይ ብርሃን የሚሰራ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋም ለአገልግሎት መብቃቱ ውሃ ለማግኘት ያደርጉት የነበረውን ረጅም ጉዞ እንዳስቀረላቸው ገልፀዋል። በክልሉ አሁን ያለው የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ከ77 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን ይህን ለማሳደግ የተለያዩ የውሃ ተቋማት ግንባታ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው።    
በቱሪዝም ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል
Feb 26, 2026 102
አርባ ምንጭ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ የቱሪዝም ዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ አስታወቁ። የቱሪዝም ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት የዘርፉ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ እንደተናገሩት የቱሪዝም ዘርፍ ለ10 ዓመት የሀገሪቱ የልማት ዕቅድ ስኬት ወሳኝ ድርሻ ያለው በመሆኑ ሚኒስቴሩ የመካከለኛ ዘመን ዕቅድ ነድፎ እየሠራ ይገኛል ብለዋል። በሀገሪቱ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ የቱሪዝም ፀጋዎችን በመጠበቅ፣ በማልማትና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስፋፋት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጀመሩ የገበታ ለሀገርና ለትውልድ ፕሮጀክቶች በአዳዲስ እይታ በዘርፉ ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈቱ ናቸው ብለዋል።   እንደ ሀገር የቱሪዝም ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና ነባሮቹን በማጠናከር ለጎብኚዎች ክፍት መደረጉንና በዚህም ውጤት መገኘቱን ጠቅሰዋል። በርካታ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በተደረጉ ጥረቶች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ጠቅሰው ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ይሰራል ብለዋል። በፈረንጆች 2025 በቱሪዝም ዘርፍ 15 በመቶ ዕድገት መመዝገቡን አስታውሰው፣ ለዚህም የመገናኛ ብዙሃን፣ የግሉ ዘርፍ፣ የልማት አጋሮችና ሌሎች ድርሻቸው ጉልህ እንደነበር ተናግረዋል። በቀሪ ወራትም በየደረጃው ያሉ ተቋማትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማጠናከር፣ ብቁ አመራሮችና ባለሙያዎችን ለመፍጠርና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት ይሠራል ነው ያሉት። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ቱሪዝም ከብዝሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ አምዶች መካከል ለብልጽግና ጉዞ ስኬት አይተኬ ሚና እንዳለው አንስተዋል። በክልሉም ሰፊ የቱሪዝም አቅም እንዳለ ጠቁመው፤ በተለይ የረጅም ጊዜ የታሪክ፣ የድንቅ ባህል፣ የተፈጥሮ ሀብት እንዲሁም የብዝሃነት ፀጋ ባለቤት መሆኑ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ አቅም ነው ብለዋል። ከክልሉ በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቅርሶች፣ ብሔራዊ ፓርኮች እንዲሁም ባህላዊ፣ ተፈጥሯዊና ሃይማኖታዊ የቱሪዝም ሀብቶች ለሀገሪቱ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የመስህብ ስፍራዎቹን በማልማት፣ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በማስፋፋትና ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማላቅ የክልሉ መንግስት በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል ነው ያሉት። አርባ ምንጭ ከተማ በቱሪዝም ሀብቷና በሰላም እሴቷ የደመቀች በመሆኗ ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላት የገለጹት ደግሞ የከተማዋ ከንቲ መስፍን መንዛ(ዶ/ር) ናቸው። በከተማዋ እየተገነባ ያለው የገበታ ለትውልድ ኮንፍረንስ ሪዞርት ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ጠቅሰው፣ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ አበርክቶ ከፍ ለማድረግ እየተሠራ ነው ብለዋል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ አባላትን ጨምሮ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደር የዘርፉ ተጠሪዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
በክልሉ የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን የማስፋት ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Feb 26, 2026 93
ሆሳዕና ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን የማስፋት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በክልሉ የመንገዶች አስተዳደር የሆሳዕና ዲስትሪክት የተገነባው የማሬ -አቡና -መሰና -ጃጁራ የ30 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል፡፡   ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የክልሉ መንግሥት የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ተግባራትን እውን የማድረግ ስራን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በርካታ ፕሮጀክቶች ወደ ልማት እንዲገቡ ይደረጋል በተለይ የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን የማስፋት ተግባራትን አጠናክሮ በማስቀጠል ፈጣን እድገትን ለማረጋገጥ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።   ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው መንገድ ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ የአካባቢው ማህበረሰብ መሰረተ ልማቱን በአግባቡ ሊጠቀምበት ይገባል ብለዋል፡፡ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ በበኩላቸው፤ ዛሬ የተመረቀው የ30 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ በርካታ እድሎችን ይዞ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡   የተገነባው መንገድ ከምባታ ዞንን ከሀዲያ ዞን ጋር በሚያገናኙ በ11 ቀበሌያት በኩል በማለፍ ወደ 262 ሺህ የሚጠጋ ቁጥር ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል፡፡ የመንገዱ ግንባታ ከ 173 ሚሊዮን 963 ሺህ ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበትም ገልፀዋል፡፡   የመንገድ መሰረተ ልማቱ መጠናቀቅ በአካባቢው የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ለገበያ ለማቅረብ እንደሚረዳ የተናገሩት ደግሞ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ ናቸው፡፡   አካባቢው በግብርናው ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም የመንገዱ ግንባታ ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው የተናገሩት። በአካባቢው በነበረው የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር ያመረቱትን ምርት ለገበያ ለማቅረብ ይቸገሩ እንደነበር የተናገሩት ደግሞ በሀዲያ ዞን በሶሮ ወረዳ የ2ኛ በናራ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ገበየሁ ሐይሉ ናቸው፡፡   ወላድ እናቶችንና የጤና እክል የገጠማቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች ወደ ጤና ተቋም ለማድረስ ይገጥም የነበረውን ችግር ከማቃለል አንፃርም የመንገዱ ግንባታ ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖሩው ነው የጠቀሱት። በመርሐ ግብሩ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አገልግሎቶቹን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ አድርጓል
Feb 26, 2026 98
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ሥርዓት ለማቀላጠፍና ቁጥጥሩን ለማዘመን አገልግሎቶቹን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማድረጉን የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ። ኢትዮጵያ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ በርካታ ውጤታማ የዲጂታላይዜሽን ተግባራትን አከናውናለች። ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችለው ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ዲጂታል ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ነው በዲጂታል 2025 በርካታ ተቋማት አገልግሎታቸውን ያዘመኑ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በዲጂታል የተደገፈ የተቀላጠፈ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ። የጉምሩክ ኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ ዲጂታል 2025 ተከትሎ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ አተኩሮ በርካታ ውጤታማ ተግባራት በማከናወን የሚሰጡ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ ተችሏል፡፡፡ በአሁኑ ወቅት ነጋዴዎች በማንኛውም ቦታ ሆነው የጉምሩክ ሥርዓትን መፈጸም የሚችሉበት የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት መዘርጋት መቻሉን አስታውቀዋል። ከ70 በላይ ተቋማትን በአንድ ላይ የሚያገናኘው የኤሌክትሮኒክ ሲንግል ዊንዶው ፕላትፎርም ተግባራዊ መድረጉን አንስተው፤ ይህም የንግድ ስራን ለማቀላጠፍ ትልቅ እመርታ መሆኑን ተናግረዋል። የኮሚሽኑን የክትትል አቅም ለማሳደግ ስማርት ቦርደር ማኔጅመንት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ሲሉም አንስተዋል፡፡ የኤሌክትሮኒክ ካርጎ ትራኪንግ ሲስተምን በመጠቀም ጭነቶች ካለባቸው መስመር እንዳይወጡ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝም ምክትል ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል፡፡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዙ ካሜራዎች በተለያዩ ስልታዊ ቦታዎች ላይ ተተክለው ውጤታማ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ምክትል ኮሚሽነሩ ኮሚሽኑ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ከባንኮችና ከሌሎች ፈቃጅና ተቆጣጣሪ ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂ ትስስር መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡ በሀገር ውስጥ የታክስ ሥርዓትም የኢ-ፋይሊንግ እና የኢ-ፔይመንት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ ውለዋል ብለዋል። እንደ ምክትል ኮሚሽነሩ ገለጻ በአሁኑ ወቅት በጂቡቲ የሚገኙ ሁለት ቅርንጫፎችን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ ያሉ 15 ቅርንጫፎች በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የ24 ሰዓት አገልግሎት በቴክኖሎጂ በመስጠት ላይ ይገኛሉ። ይህ መጠነ ሰፊ የዲጂታላይዜሽን ስራ የገቢና ወጪ ንግዱን ከማሳለጡ ባለፈ፣ የህግ ማስከበር ስራውን በቴክኖሎጂ የታገዘና ግልጽ አሰራረን ተግባራዊ በማድረግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚደግፍ አስታውቀዋል።
እያደገ የመጣው የአማራጭ ኢነርጂ ቴክኖሎጂ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል
Feb 26, 2026 45
ደብረ ማርቆስ ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን እያደገ የመጣው የአማራጭ ኢነርጂ ቴክኖሎጂ ተደራሽነት የዜጎች ኑሮ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱ ተገለጸ። የገጠር መሬትን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር አርሶአደሩ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ ነው ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የምስራቅ ጎጃም ዞን አርሶ-አደሮች፤ አማራጭ ኢነርጂ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀማቸው የደን ጭፍጨፋን መቀነስ፣ ጤናቸውን መጠበቅና ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። የጎዛምን ወረዳ ደሳ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጌታቸው አንሙት፣ የባዮጋዝ ቴክኖሎጂን በመገንባት ለምግብ ማብሰያና ለመብራት አገልግሎት መጠቀም መጀመራቸውን ተናግረዋል። ይህም ቀደም ሲል ለማገዶና ለናፍጣ ሳወጣ የነበረውን ወጪ ቆጥቦልኛል ብለዋል። አማራጭ የኢነርጂ ቴክኖሎጂው የእርሳቸውንና ቤተሰባቸውን ጤና እንዲጠብቁ ከማድረግ ባለፈ ማገዶ ፍለጋ ጫካ በመሄድ ይደረስባቸው የነበረውን እንግልት መቀነሱን ገልጸዋል። አርሶ አደር ጌታሁነኝ ብርሃን በበኩላቸው፣ ከባዮጋዝ የሚገኘውን ተረፈ ምርት እንደ ማዳበሪያ በመጠቀማቸው የአትክልትና ሰብል ምርታማነታቸው መጨመሩን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂውን ለተለያዩ አገለግሎቶች እያዋሉት መሆኑንና በዚህም በኑሯቸው ላይ ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን አንስተዋል። የእነደድ ወረዳ ነዋሪ ዘውዲቱ ጥላሁን፣ ዘመናዊና ሀይል ቆጣቢ ምድጃዎችን መጠቀም መጀመራቸው ከዚህ ቀደም በእሳት ነበልባልና በጭስ ምክንያት ይደርስባቸው ከነበረው የጤና መታወክ እንደታደጋቸው ገልጸዋል። የምስራቅ ጎጃም ዞን ውሃና ኢነርጅ መምሪያ ሃላፊ ፍሬው ካሴ እንደገለጹት፤ በዞኑ አማራጭ ኢነርጂ ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን በማስፋት የአርሶአደሩን ኑሮ ለማሻሻል ጥረት እየተደረገ ነው። በ2018 በጀት ዓመት ከ44ሺህ በላይ የተለያዩ የአማራጭ ኢነርጂ ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አስታውሰው፣አሁን ላይ ከ34 ሺ በላይ ቴክኖሎጂዎች ለአርሶ አደሩ ተደራሽ መደረጋቸውን ተናግረዋል። ከአማራጭ የሃይል ቴክኖሎጂዎች ውስጥ 21 ሺህ 243ቱ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎች፣ 13 ሺህ 451ዱ በጸሃይ ሃይል የሚሰሩና 261ዱ የባዮጋዝ ቴክኖሎጂ ግንባታ ይገኙበታል ብለዋል። በቴክኖሎጂዎቹ ከ140 ሺ በላይ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መሆናቸውንና በዚህም የደን ጭፍጨፋን መከላከልና የሕብረተሰቡን ጤና መጠበቅ እንደተቻለ አመልክተዋል። በዞኑ እስካሁን አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ የተለያዩ የአማራጭ ኢነርጂ ቴክኖሎጂዎች ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆናቸውን የመምሪያው መረጃ ያመለክታል።
የሰውሰራሽ አስተውሎት ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው
Feb 26, 2026 62
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ የሰውሰራሽ አስተውሎትና የዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ። በትምህርት ሚኒስቴር የኢ-ለርኒንግና የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ አስተባባሪ ሙሉነህ አጥናፉ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በሀገሪቱ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ስራዎችን ለማሳለጥና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ ውጤታማነት የሰው ኃይል ልማት ወሳኝ ነው። የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ ነው ለዚህም የዲጂታል ክህሎትና እውቀትን ማበልፀግ እንደሚያስፈልግ አንስተው ሚኒስቴሩ ሀገራዊ የሪፎርም አጀንዳዎችንና ተልዕኮውን መሰረት ያደረገ ጉዞ መጀመሩን ተናግረዋል። የመምህራንና ተማሪዎችን እንዲሁም የህብረተሰቡን የዲጂታል እውቀትና ክህሎት ማሳደጊያ መርኃ ግብሮችን ለመተግበር እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ የሆነው የሰውሰራሽ አስተውሎት መሆኑን አንስተው ዘርፉ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን ጠቀሜታ ማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። የሰውሰራሽ አስተውሎትና የዲጂታል ግንዛቤን የሚያሳድግ ትምህርት ከአንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ በስርዓተ ትምህርት ውስጥ በማካተት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራንና ተማሪዎችን የዲጂታል ክህሎትና እውቀት ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ለዚህም የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጨምረው አስረድተዋል። ትምህርት ሚኒስቴር ከዲጂታሉ ዓለም ጋር ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው የሚራመዱ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን ለማፍራት የዲጂታል እውቀትና ክህሎት መሠረቶች ላይ ትኩረት መስጠቱንም ገልጸዋል፡፡
ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው
Feb 26, 2026 95
አሶሳ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ አስተባባሪ ደጀኔ ገብሬ አስታወቁ። በ2014 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የተጀመረው የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር በማስተሳሰር የዲጂታል መሠረተ ልማትን ለማሳለጥ እየተሰራ ይገኛል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ160 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ደምበኞች የተቀላጠፈ አገልግሎት ተሰጥቷል የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ አስተባባሪ ደጀኔ ገብሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ አካታች እንዲሆን ከተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በቅንጅት እንዲሰራ ተደርጓል። በዚህም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን ገልፀው፤ የምዝገባ ፕሮግራሙ ከተጀመረ ወዲህ 36 ሚሊዮን ዜጎች ተመዝግበው የመታወቂያው ባለቤት መሆናቸውን ገልጸዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የአገልግሎት አሰጣጥን የሚያቀላጥፍ እና ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ዓይነተኛ ሚና እያበረከተ እንደሆነ ጠቁመው፤ በተለይም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ከግብ ለማድረስ ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። ለአብነትም ፋይዳን ከአርሶ አደሩ የመሬት ባለቤትነት ጋር ማስተሳሰር በርካታ ዜጎች እንዲመዘገቡ ከማድረግ ባለፈ አርሶ አደሩ ይዞታውን አስይዞ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኝ እና ማሳውን በአግባቡ ለማስተዳደር እንደሚያግዘው አንስተዋል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስካሁን ከ250 ሺህ በላይ ዜጎች የተመዘገቡ ሲሆን አፈጻጸሙን ለማሻሻል የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ እንደሚያስፈልግም አስተባባሪው አስታውቀዋል። በክልሉ የመቶ ፐርሰንት ግብ አፈጻጸም ዝቅተኛ በመሆኑ ከተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በማስተሳሰር ዕቅዱን ማሳካት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሬትና ህብረት ስራ ማደራጃ ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "ብሔራዊ መታወቂያ ለገጠር መሬት ባለይዞታዎች" በሚል መሪ ሃሳብ የምክክር መድረክ መካሄዱ ይታወሳል።
ስፖርት
ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ አብሮነትና ወንድማማችነትን ያጎለብታሉ
Feb 26, 2026 15
ወልቂጤ ፤የካቲት 19/2018(ኢዜአ) :- ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ አብሮነትና ወንድማማችነትን ለማጎልበት እንደሚያስችሉ ተመላከተ። በወልቂጤ ከተማ ለተከታታይ 10 ቀናት ሲካሄድ የቆየው 3ኛው የክልል አቀፍ ሻምፒዮናና የባህል ስፖርቶች ውድድር ፌስቲቫል ተጠናቋል፡፡ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሶ፤ በወቅቱ እንዳሉት ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ አብሮነትና ወንድማማችነትን ያጎለብታሉ።   በ17 ዘርፎች የተካሔደው ስፖርታዊ ውድድሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመወዳደር የሚችሉ ስፖርተኞች የተለዩበት እንደሆነም ገልፀዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ በዋናነትም በዘርፉ የወጣቶችን ተሰጥኦ ለመለየት እገዛው የጎላ እንደነበርም ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት በዘርፉ የሚፈገለውን ውጤት ለማምጣት የስፖርት ማዘውተሪያ መሰረተ ልማቶችን ከመገንባት ባሻገር ስፖርታዊ ጨዋነትን የሚያሳድጉ ተግባራት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው፣ መርሃ ግብሩ የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን በማጎልበት በተሻለ መንገድ አንድነትን ለመፍጠር ያስቻለ መሆኑን ጠቅሰዋል።   ስፖርታዊ ውድድሩ በአካባቢው ላይ መነቃቃትን የፈጠረ ሲሆን የባሕል እሴቶችንም ለማስተዋወቅ ትልቅ እገዛ አድርጓል ነው ያሉት። ታዳጊ ወጣቶችን ለማፍራት የተከናወኑት ተግባራት አዳዲስ እና ተተኪ ስፖርተኞች የተገኙበት መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ የስፖርት ትምህርት ስልጠና ባለሙያ አቶ ባዘዘው ደምሴ ናቸው ። በዞኑ በተዘጋጀው የውድድር መርሃ ገብር ላይ በ17 ዓይነት የውድድር ዘርፎች ተወዳዳሪዎችን ማሳተፍ መቻሉን ጠቅሰው ይህም መንግስት ለስፖርቱ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት ያመላክታል ብለዋል። የጠንባሮ ልዩ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት የስፖርት ተሳትፎና ውድድር ቡድን መሪ አቶ አባይነህ ጎበዜ በበኩላቸው፤ በክልሉ በስፖርት ዘርፍ የተጀመረውን ሥራ ለማጠናከር እየተደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ከክልል ጀምሮ በየደረጃው ያሉ ኃላፊዎችና የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በስፖርታዊ ውድድሩ የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች የሜዳሊያ፣ የዋንጫና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።
ወላይታ ድቻ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ 
Feb 26, 2026 40
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ጨዋታዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ወላይታ ድቻ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። ካርሎስ ዳምጠው ግቦቹን አስቆጥሯል። የድሬዳዋ ከተማው ድልአዲስ ገብሬ በ51ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። በሊጉ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ወላይታ ድቻ በ22 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በሊጉ አራተኛ ደረጃን ይዟል። በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ25 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሐ ግብር አዳማ ከተማ እና ሸገር ከተማ ሶስት አቻ ተለያይተዋል።   ለአዳማ ከተማ አላዛር ሽመልስ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር አህመድ ሁሴን ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጀቤሳ ሚኤሳ እና ቢንያም ፍቅሩ በጨዋታ ሄኖክ አዱኛ በፍጹም ቅጣት ምት ለሸገር ከተማ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። አዳማ ከተማ በ32 ነጥብ አምስተኛ፣ ሸገር ከተማ በ23 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዘዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በሀዋሳ በፕላስቲክ ከረጢት ምትክ አማራጭ ምርቶችን የመጠቀም ልምድ እየዳበረ ነው
Feb 26, 2026 167
ሀዋሳ ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- በሀዋሳ ከተማ በፕላስቲክ ከረጢት ምትክ አማራጭ ምርቶችን የመጠቀም ልምድ እየዳበረ መምጣቱን የከተማ አስተዳደሩ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ጽህፈት ቤት ገለፀ፡፡ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 መሠረት እንደ ሀገር ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የፕላስቲክ ከረጢት ማምረት፣ ወደ ሀገር ማስገባት፣ መሸጥና መጠቀም ላይ ክልከላ ተደርጓል፡፡ አዲስ አበባ በንፅህና አጠባበቅ ረገድ እያከናወነች ያለው ሥራ በአርዓያነት ይጠቀሳል ባልተገባ መልኩ የሚጣሉ የፕላስቲክ ከረጢቶች /ፌስታል/ አካባቢን በመበከል፣ የውሃ መስመሮችን በመዝጋት፣ በተለይ ሳይበሰብሱ ለብዙ ዓመታት በመቆየት የስነ ምህዳር ጠንቅ እንደሆኑ ሳይንሳዊ ምርምሮች ያወሳሉ።   በኢትዮጵያ የፕላስቲክ ከረጢት አጠቃቀምን ለመገደብና ለመከልከል ባለፉት ዓመታት በርካታ ጥረቶች ሲደረጉ የቆዩ ሲሆን ክልከላው በዋናነት የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስና የህዝብን ጤና ለመጠበቅ ያለመ መሆኑም ይታወቃል። ይህንን ተከትሎ በሀዋሳ ከተማም ክልከላው ተግባራዊ እየተደረገ ሲሆን በህብረተሰቡ ዘንድ በፕላስቲክ ከረጢት ምትክ አማራጭ ምርቶች የመጠቀም ልምድ እየዳበረ መምጣቱን የጽህፈቱ ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ሹምባሻ ለኢዜአ ገልጸዋል፡፡   ጽህፈት ቤቱም ክልከላውን ከማስተግበር ጎን ለጎን ምትክ ምርቶች በስፋት ለሕብረተሰቡ እንዲቀርቡ እየሰራ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት በከተማዋ 15 ድርጅቶች ምትክ የወረቀት ከረጢቶችን በማምረት ሥራ ላይ በመሰማራታቸው አዋጁን ከመተግበር ባለፈ ለዜጎች የስራ እድል መፍጠር ችለዋል ብለዋል። የኤሊያና ፔፐር ፓኬጂንግ ኤንድ ማኑፋክቸሪንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረጀ ሞገስ በበኩላቸው፤ ድርጅታቸው የወረቀት ከረጢቶችን በስፋት የማምረት ስራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡   አዋጁ ስነ ምሕዳሩን ከመጠበቅ ባለፈ በዘርፉ ተጨማሪ የገበያ ዕድል በማስገኘት ሰፊ አስተዋጽኦ አበርክቷል ነው ያሉት። በአሁኑ ወቅትም 85 ወጣቶችን በማሰልጠን የስራ እድል ለመፍጠር የተቻለ ሲሆን በቀን እስከ 15 ሺህ የወረቀት ከረጢቶችን እያመረቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሱፐር ማርኬት ሥራ ላይ የተሰማሩት ወይዘሮ ፀሐይ ይርዳው በበኩላቸው፤ የጨርቅ ከረጢቶችና ካርቶኖችን በመጠቀም ደንበኞቻቸውን እያስተናገዱ እንደሚገኙ ይገልፃሉ።   ከዚሁ በተጨማሪም ማህበረሰቡ አምኖበት የወረቅ ምርቶቹን እንዲጠቀም ለማድረግም ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየሰሩ መሆኑን ነው ያነሱት። በሆቴል ሥራ ላይ የተሰማሩት ወይዘሮ ልደት ማሩፋ፤ የፕላስቲክ ከረጢት ክልከላው ሀዋሳን ፅዱ ከማድረግ ባለፈ ሀይቁን ከብክለት ሥጋት ነፃ የሚያደርግ በመሆኑ በደስታ እንደተቀበሉት ገልፀዋል፡፡   ለቤታቸው በሚሸምቱት ዕቃም ሆነ በሆቴል አገልግሎታቸው አማራጭ ምርቶችን ብቻ እየተጠቀሙ መሆኑን ተናግረው የክልከላ አዋጁ ተግባራዊ እንዲሆንና ፅዱ ከተማን ለመፍጠር ሁሉም መተባበር እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በታዳሽ ኃይል ለዓለም የስኬት አርዓያ ሆናለች -የሮማኒያ አምባሳደር
Feb 25, 2026 109
አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በታዳሽ ኃይል ለዓለም የስኬት አርዓያ ሆናለች ሲሉ በኢትዮጵያ የሮማኒያ አምባሳደር ጁሊያ ፓታኪ ገለጹ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቀጣናውን በሀይል በማስተሳሰር ረገድም ጉልህ ፋይዳ እንዳለውም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት ባለፉት ዓመታት በተገበረችው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ችላለች። ይህ ተግባርም የዓለም የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል የተስተካከለ ምህዳርን ለመፍጠር ጉልህ ሚና አለው። ኢትዮጵያ በዚህ ተግባሯም ዓለም አቀፍ እውቅናዎችን አግኝታለች። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ የሮማኒያ አምባሳደር ጁሊያ ፓታኪ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ልማት ለማሳደግ እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ ስኬቶች ሀገሪቷን በዓለም ላይ እውቅና እያስገኘላት መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ድንቅ የአካባቢ ጥበቃ ስራ መሆኑን ጠቁመዋል፤የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር መረጃዎችን እያስፋፋን ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ እየተገበረችው ያለው የአረንጓዴ አሻራ ስኬቶች ሀገሪቷን በአረንጓዴ ልማት፣ በታዳሽ ሀይል ስራዎች ለሌሎች ሀገራት አርዓያ አድርጓታል ብለዋል። አምባሳደሯ አክለውም ኢትዮጵያ በልማት ጎዳና ላይ መሆኗን ጠቁመው፤ በአዲስ አበባ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተመዘገቡ ያሉ የልማት ውጤቶች የሚደነቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህ የልማት እንቅስቃሳም በሌሎች የክልል ከተሞች እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል። የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶችን ጨምሮ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች አዲስ አበባን እውነተኛ የአፍሪካ መዲናነቷን በተግባር ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው በአፍሪካ ልዩ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ግድቡ ቀጣናውን በሀይል በማስተሳሰር ረገድም ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።
የበልግ እርሻ እንቅስቃሴን ቀድመው የሚጀምሩ አካባቢዎች፣ በሚቀጥሉት ስምንት ቀናት የሚኖረውን የእርጥበት አየር ሁኔታ በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል 
Feb 23, 2026 119
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦የበልግ እርሻ እንቅስቃሴን ቀድመው የሚጀምሩ አካባቢዎች፣ በሚቀጥሉት ስምንት ቀናት የሚኖረውን የእርጥበት አየር ሁኔታ በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አሳሰበ። ኢንስቲትዩቱ ከየካቲት 14 እስከ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የሚኖረውን የአየር ሁኔታ አስመልክቶ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፤ በሚቀጥሉት ቀናት በበልግ አብቃይ አካባቢዎች ላይ አንጻራዊ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚኖር ገልጿል። በተለይም በደቡብ ምዕራብ፣ በደቡብ እና በመካከለኛው ዝቅተኛ አካባቢዎች የሚታየው እርጥበት፤ ለአፈር ዝግጅት፣ ለዘር ዝግጅትና ለዘር መዝራት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ብሏል። የሚገኘው እርጥበት ለግጦሽ ሳር በቀል፣ ለቋሚ ተክሎች እድገትና ለሰውና ለእንስሳት የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማሻሻል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም አመልክቷል፡፡ በላይኛው አዋሽ፣ በላይኛውና በመካከለኛው ባሮ አኮቦ፣ በኦሞ ጊቤ፣ በስምጥ ሸለቆ እንዲሁም በጥቂቱ በላይኛው ገናሌ ዳዋ ተፋሰሶች ላይ ከመካከለኛ እስከ መጠነኛ ዝናብ እንደሚጠበቅም ተመላክቷል፡፡ በዚህም ምክንያት በተጠቀሱት ተፋሰሶች ላይ መጠነኛ የገፀ-ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖር ተመላክቷል። በሌላ በኩል የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች ላይ ደረቃማ ቀናት እንደሚስተናገዱ በመግለጫው ተጠቅሷል።    
የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የቡና ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ትልቅ ለውጥ ፈጥሯል
Feb 23, 2026 254
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የቡና ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ትልቅ ለውጥ ፈጥሯል ሲሉ የዘርፉ ተዋናዮች ገለጹ። ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት 469 ሺህ ቶን ቡና ለዓለም ገበያ በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቷ የሚታወስ ሲሆን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት 600 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጪ በመላክ ከሦስት ቢሊየን ዶላር በላይ ለማግኘት አቅዳ እየሰራች ትገኛለች፡፡ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት በግብርናው ዘርፍ የቡና ምርታማነት ላይ አመርቂ ውጤት ለማስመዝገብ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ወሳኝ መሆኑን ያረጋግጣሉ።   በኦሮሚያ ክልል የቡና አልሚና ላኪ የሆኑት አቶ ፈጠነ የኋላሸት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ በተለይ አረንጓዴ አሻራ ትልቅ አስተዋጾ ማበርከቱን ተናግረዋል ባለፉት ዓመታትም የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር በተከታታይነት መከናወኑ ቡናን ለማምረት ተስማሚ ሥርዓተ ምህዳርና የአየር ሁኔታ እንዲኖር ማስቻሉን ነው ያነሱት። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በቡና መስክ ላይ የተሰማሩት አንዷለም ፋንታ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ ለውጥ እያመጣ ነው ብለዋል።   ይህም በመሆኑ በአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ላይ የማህበሩ አባላት በስፋት በመሳተፍ ልማቱን እያገዝን እንገኛለን ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል። በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የቡና ምርታማነታችንን ለማሳደግ የአካባቢውን የተፈጥሮ ገጽታ መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በሲዳማ ክልል በቡና አቅራቢነት የተሰማሩት አባተ ኪሾ ናቸው ።   አስተያየት ሰጪዎቹ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን እና ዝርያዎችን ለተከላ ለማዘጋጀት የሚያስችላቸውን ተግባር እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡና ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ዘሪሁን ቃሚሶ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ሀገራችን ከቡናው ዘርፍ ማግኘት የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማሳለጥ ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።   አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እንደ ሀገር ማከናወን ከጀመርን በኋላ ከ8 ቢሊየን በላይ የቡና ችግኞች መተከላቸውን አስታውቀዋል።    
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Feb 23, 2026 111
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ በሰላም፣ ልማት እና ዲፕሎማሲ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ(ኢ/ር) ከተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አፍሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ ለረጅም ጊዜ የቆየ እና ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው ትብብሩ በጥልቅ የባህል፣ የኢኮኖሚና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ላይ የተመሰረተ መሆኑን አውስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ በአፍሪካ ያላትን ዘላቂ ትብብር እና በአህጉሪቱ እያደገ የመጣውን ኢንቨስትመንት አልፎም በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ያላትን ገንቢ ሚና አድንቀዋል።   ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመቀናጀት በሊቢያ፣ ሱዳን እና ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች እያሳየች ያለውን የዲፕሎማሲ ድጋፍ እና ተሳትፎ አዎንታዊ መሆኑን አመልክተዋል። የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ በበኩላቸው የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ በልማት፣ በሰላም እና በባለብዙ ወገን ትብብር ያለውን የመሪነት ሚና አንስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ልማት፣ ሰላም፣ ደህንነት እና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላትን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የአፍሪካ ህብረትና ሳዑዲ አረቢያ ያላቸውን ግንኙነት በጋራ መከባበር መንፈስ፣ በወዳጅነት እና በስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ በመመስረት የበለጠ ለማጠናከር የጋራ ፍላጎት ማሳየታቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና የፈጠረውን የንግድ ትስስር ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 165
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን የንግድ ትስስር ዕድል በአግባቡ ለመጠቀም በመንግሥታትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለ አጋርነትን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ።   የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የስምምነቱ ትግበራ የንግድ መሰናክሎችን በማስቀረት የሀገራትን የንግድ ልውውጥ ለማሳለጥ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ ነው። እስካሁን 50 ሀገራት ፈርመው ያጸደቁት ይህ የንግድ ቀጣና፤ በዲጂታል የኢኮኖሚ ዕድገት የፋይናንስ ቴክኖሎጂን በማስፋት የአኅጉሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በማዘመንና የገንዘብ ዝውውርን በማቀላጠፍ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት የአሰራር ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተዳራሽ ለማድረግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ዘርግቷል የኢትዮጵያ ቱሪዝም አዲሱ ገጽታ፤ ከአማራጭ ማጣት ወደ መዳረሻዎች ብዛት በኢትዮጵያ ለግል ዘርፉ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ኢኮኖሚው እየተነቃቃ ነው የአፍሪካን የተፈጥሮ ሃብትም በተሻለ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነት በማልማት የመሰረተ ልማት፣ የዋጋ ግሽበትና የንግድ መሰናክሎችን ለመቀነስ አይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም አስረድተዋል።   በዚህም አባል ሀገራት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን በማፋጠን የእርስበርስ የንግድ ልውውጥን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን ዕድል ለመጠቀም የግሉ ዘርፍና የአባል ሀገራት መንግሥታት የእርስ በርስ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሰረትም የአባል ሀገራት ኢንቨስትመንትን የሚያነቃቃ የኢንቨስትመንት ጥበቃ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስረድተዋል። የስምምነቱ የኢንቨስትመንት ጥበቃም የአፍሪካን በመተማመን ላይ የተመሰረተ የእርስበርስ ንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን አስታውቀዋል።
ሐተታዎች
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 153
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።      
   የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 183
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን።   የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው።   የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል።   የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት።   የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 629
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ።   በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 966
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 166
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 278
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1037
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 998
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3517
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2338
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8131
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6616
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60360
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54323
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34910
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32478
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27680
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26712
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26230
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25974
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60360
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54323
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34910
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32478
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ የስኬት ጉዞ …
Feb 26, 2026 108
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ በየዘርፉ እያስመዘገበቻቸው የሚገኙት ስኬቶች በተለያዩ የዓለም መድረኮች በምሳሌነት እያስጠቀሳት ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በአምስቱ ዋና ዋና የኢኮኖሚ አምዶቿ ማለትም በግብርና፣ በኢንዳስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን ቀጥለን እንዳሥሣለን። የስንዴ ምርታማነት ስኬት ኢትዮጵያ በግብርና በተለይ በሌማት ትሩፋት እና በስንዴ ልማት ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ ስኬት ያስመዘገበችባቸው መስኮች ናቸው። ቀደም ሲል ስንዴን ከውጭ ለማስገባት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ታወጣ እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከለውጡ መንግስት ወዲህ ግን በተለይ ለስንዴ ልማት በተሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የግብርና ሜካናይዜሽን በመጠቀም ምርት እና ምርታማነትን በከፍተኛ መጠን ማሳደግ በመቻሉ ከራስ ፍላጎት ባለፈ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ላይ ትገኛለች። ይህ ውጤታማነቷም በተለያዩ የዓለም ዓቀፍ ተቋማት ጭምር እውቅና አስችሯታል። ለስንዴ ምርት እና ምርታማነት ማደግ ዘመናዊ የመስኖ ሥርዓቶች፣ የኩታ ገጠም አስተራረስ ዜዴ፣ የግብርና ሜካናይዜሽን ስልቶችና የግብርና ኢኒሼቲቮች በዋና ምክንያትነት ይጠቀሳሉ። በዚህ መነሻነት ነው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ የኢትዮጵያ የስንዴ ምርታማነት ለአፍሪካ አርዓያነት ያለው መሆኑንና በስንዴ ልማት ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ያስመዘገበችው ለውጥ ከፍተኛ መነሳሳት መፍጠሩን ጠቅሰዋል። ይህን የኢትዮጵያን ውጤታማነት መነሻ በማድረግም የአፍሪካ ሀገራት እንዲተገብሩት መክረዋል። በተመሳሳይ በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ መሸለማቸው ይታወቃል። ሽልማቱ በምግብ ዋስትናና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ትጋት፣ ፈጣን፣ ተለዋዋጭና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ ዕውቅና ለመስጠት የተበረከተ ነው። የኢትዮጵያ የስንዴ ምርታማነት ስኬት የግብርናው አብዮት ማሳያ ሲሆን፤ ራስን መቻል እና ለአፍሪካ መብቃትን ያለመ ነው። ዲፕሎማሲያዊ ስኬት   በሰላም ግንባታ፣ ግጭት አፈታት እና አኅጉራዊ ትሥሥር ረገድ ሚናዋን እየተወጣች ያለችው ኢትዮጵያ፤ በዲፕሎማሲው መድረክም ተደማጭነቷ እያደገ መጥቷል። በሰላም ማስከበር፣ አረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች ዐበይት ጉዳዮች ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜያት በዓለም መድረኮች ስሟ ከፍ ብሎ እየተሰማ ነው።   የቱርክዬ ፕሬዚዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን፣ የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይ፣ የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳው፣ የእስራኤል ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ እና የሌሎች ሀገራት ባልሥልጣናት የቅርብ ጊዜ የኢትዮጵያ ጉብኝቶች የሀገሪቱን የጂኦ ፖለቲካዊ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ብሎም የዲፕሎማሲ ተደማጭነት እያደገ መምጣት ያሳያሉ። ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክ ብሔራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ ባለፈ በዓለም መድረክ የአፍሪካ ድምጽ እየሆነች ትገኛለች።   አረንጓዴ ዐሻራ - ሌላኛው የኢትዮጵያ ስኬት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት በሀገር አቀፍ ደረጃ ሐምሌ 2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር፤ እስከአሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። በ2011 ዓ.ም 17 ነጥብ 2 በመቶ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን፤ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ በተከናወነው ሥራ አሁን ላይ ከ23 በመቶ በላይ ደርሷል። በኢትዮጵያ በተካሄደው 2ኛው የዓለም የምግብ ሥርዓት ጉባዔ የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራው ዕውቅና ተችሮታል። በተጨማሪም በ2ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባዔ የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራዋን ኢትዮጵያ ባስተዋወቀችበት ወቅት፤ የአፍሪካ ሀገራት ትልቅ ተምሳሌት የሚሆን ኢኒሼቲቭ መሆኑንም በምሳሌነት ጠቅሰውታል። ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ችግኝ በመስጠት የአካባቢ ጥበቃ የጋራ አጀንዳ መሆኑን አሳይታለች። ይህም "አረንጓዴ ዲፕሎማሲ" በመባል የሚታወቅ ሲሆን፤ በሀገራት መካከል በጎ ግንኙነትን ለማዳበር አስተዋጽኦ አበርክቷል።   የግዙፍ (ሜጋ) ፕሮጀክቶች ግንባታና ምረቃ በወርሃ ጳጉሜን 2017 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለአፍሪካ የኢነርጂ ትሥሥር ውጥን ትልቅ የምሥራች ነው። የጎረቤት ሀገራት ከኢትዮጵያ የሚያገኙት የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦትም ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር ያስችላል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙ የሀገራት መሪዎች ባደረጉት ንግግር የሕዳሴ ግድብ የአፍሪካ ራስን የመቻል ምልክት እና የኢትዮጵያ አይበገሬነት ተምሳሌት መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የኒውክሌር ማበልጸጊያ እንደሚገነባ፣ የጋዝ ፋብሪካ እንደሚመረቅ፣ የነዳጅ ማጣሪያ ዕውን እንደሚሆን፣ በአፍሪካ ግዙፍ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደሚገነባ፣ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶች ግንባታ እንደሚከናወን ጉባ ላይ ማብሠራቸው ይታወሳል።   ይህን ተከትሎም በሶማሌ ክልል የጋዝ ፋብሪካ ተመርቋል፣ የቢሾፍቱ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም ተጀምሯል። የሌሎች መሠረተ ልማቶች ግንባታ እና የዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። እየተገነባ ያለው ኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫም ለኢነርጂ አቅርቦት ዕድገት የበኩሉን ሚና እንደሚጫወት መገለጹ ይታወሳል።   የኮሪደር ልማት እና የከተማ ማዘመን ሥራዎች የኮሪደር ልማት ኢኒሼቲቮች የትራንስፖርትን ጨምሮ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች እንዲዘምኑ፣ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች እንዲስፋፉ፣ የንግድ ተቋማት አሰራር እንዲዘምን፣ አምፊ ቴአትርን ጨምሮ የኪነ-ጥበብ መሠረተ ልማቶች እንዲገነቡ፣ የስፖርት መሠረተ ልማቶች ግንባታ እንዲከናወን የራሳቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኮሪደር ልማቱ አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ የክልል ከተሞችን ከማስዋብ ባለፈ ዜጎች በንጹህ አካባቢ እንዲኖሩ አስችሏል። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይ ኤም ኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ እ.አ.አ በ2025 ስለ አዲስ አበባ ሲናገሩ፤ ከተማዋን ጊዜ ወስደው መመልከታቸውንና ከፍተኛ መሻሻል እንዳዩ መግለጻቸው አንዱ ማሳያ ነው። የኬንያ የፓርላማ አባል ጁኔት መሐመድም አዲስ አበባን የአፍሪካ አዲሷ ዱባይ ሲሉ አድንቀው፤ አዲስ አበባ እያስመዘገበች ያለው ፈጣን ዕድገት ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ምሳሌ መሆኑንም ገልጸዋል። በተጨማሪም የተለያዩ ዲፕሎማቶች፣ የውጭ ሀገር ዜጎች እንዲሁም የልማት አጋሮች ለአዲስ አበባ የከተማ መዘመንና ለውጥ ምስክርነታቸውን መስጠታቸው አይዘነጋም።   በሰው ሠራሽ አስተውሎት ረገድ ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂና ሰው ሠራሽ አስተውሎት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ከአምስት ዓመታት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን አቋቁማ ወደ ሥራ ገብታለች። በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠም ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን አስመልክቶ ባካሄደው መድረክ ላይ፤ ፈጥነን ልጆቻችንን ካዘጋጀን ሰው ሠራሽ አስተውሎትን እንደ ተለያዩ ምርቶች በቀላሉ መጠቀም እንችላለን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። ለሰው ሠራሽ አስተውሎት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ የምትገነባው የኤ አይ ዩኒቨርሲቲም የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ብዙ ችግሮችን ይፈታል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለሰው ሠራሽ አስተውሎት መሠረት እየጣለች መሆኗንም አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ዘመኑን የዋጀ ዕይታ ለዲጂታል ዘመን ለውጦች ምላሽ ከመስጠት ባለፈ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትንም ይፈጥራል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኢትዮጵያ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት ኢትዮጵያን በዲጂታል ዘርፉ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ የማሸጋገር ዐቅም አላቸው።   ኢትዮጵያ - የአፍሪካ የአቪዬሽን ማዕከል የአፍሪካ አቪዬሽን ምልክት የሆነው ግዙፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ ኢትዮጵያን ከቀሪው ዓለም እና አፍሪካን ርስ በርስ በማገናኘት በኩል የመሪነት ሚናውን እየተወጣ ነው። የአየር መንገዱ የመንገደኞች እና የካርጎ አገልግሎቶች የንግድ፣ የቱሪዝም እና ዓለምአቀፍ የቢዝነስ ግንኙነቶች እንዲጠናከሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተም ይገኛል። በተያዝው በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽም አየር መንገዱ 10 ነጥብ 64 ሚሊየን ሰዎችን ማጓጓዝ መቻሉ ለመሪነቱ ትልቅ ማሳያ ሆኖ ይወሰዳል። በሌላ በኩል በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ቢሾፍቱ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጀምሯል። የዚህ ግንባታ መጀመር ኢትዮጵያ በአፍሪካ አቪዬሽን ያላትን የመሪነት ሚና አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁነኛ ሚና አለው።   ሌላኛው የኢትዮጵያ ስኬት - ቱሪዝም ኢትዮጵያ በታሪክ፣ ባህል፣ በተፈጥሯዊ እና ሰው ሠራሽ የቱሪዝም መዳረሻዎች የታደለች ናት። እነዚህም ጎብኚዎችንና ተመራማሪዎችን መሳባቸውን ቀጥለዋል። መንግሥት እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ ወስዶ እየሠራበት በሚገኘው የቱሪዝም ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች ተገኝተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት፤ በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ አማካኝነት የተከናወኑ ሥራዎች የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እያሳደጉም ይገኛሉ። በቅርቡ በሶማሌ ክልል የተመረቀው እና የገበታ ለትውልድ ሥራ አካል የሆነው የሸበሌ ሪዞርት የዚሁ ሥራ ማሳያ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በምረቃው ወቅት፤ ሪዞርቱ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የገባነውን ቃል በተግባር ያረጋገጠ የምሥራቁ የሀገራችን ክፍል ትልቅ ሥራ ነው ማለታቸው ይታወሳል። በአዲስ አበባ የሚገኙት የወዳጅነት ዐደባባይ፣ አንድነት ፓርክ፣ ሳይንስ ሙዚየም እና ሌሎችም ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻዎች ሆነዋል። የኮሪደር ልማቱም የመዲናዋን መልክ በአዲስ ሁኔታ በመግለጥ ጎብኚዎችን እየሳበ ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ በግብርና፣ በዲፕሎማሲ፣ በኢኖቬሽን፣ በመሠረተ ልማት፣ በከተማ ማዘመንና ኮሪደር ልማት፣ ቱሪዝምን ጨምሮ በሌሎች መስኮች ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች የራሷን መጻኢ ጊዜ ብሩኅነት ያመላክታሉ። የኢትዮጵያ ስኬቶች ብሎም ስትራቴጂካዊ ራዕይ ጊዜውን የሚመጥን ዕድገትን በትጋትና በጋራ ትብብር የመሥራት ውጤትን የሚያሳዩ ናቸው። ኢትዮጵያ ለዛሬ ብቻ እየሠራች አይደለም፤ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሠረት እየጣለችም እንጂ።
የኢትዮጵያ ዐሻራ ከዓድዋ - እስከ አፍሪካ ኅብረት
Feb 14, 2026 328
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የፖለቲካ፣ የታሪክ እና ዲፕሎማሲ ምኅዳር ውስጥ ልዩ ስፍራ እና ተጽዕኖ ያላት ሀገር ናት። የጥንታዊ ሥልጣኔዎች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ፤ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ የአፍሪካ ሀገር ከመሆኗ ባሻገር ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ መስፋፋት ትልቅ ሚና ተጫውታለች። ይህንም ታሪክ ይዘክራል። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ ይጀመራል አይበገሬነት፣ ሉዓላዊነት እና የፓን አፍሪካ መንፈስ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ካሳረፈቻቸው ዐሻራዎች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። በዘመናዊው ዓለምም በአፍሪካ አጀንዳዎች ላይ ወሳኝ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነጻነት እና ማንነት ተምሳሌት ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1896 በዓድዋ ጦርነት በጣሊያን ኃይሎች ላይ የተቀዳጀችው ድል በአፍሪካ እና በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠው ነው።   አብዛኛው የአፍሪካ አኅጉር በቅኝ ግዛት ውስጥ በነበረበት ወቅት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ድል ሉዓላዊነቷን ከማስጠበቅ ባለፈ በአፍሪካ እና በአፍሪካ ዳያስፖራ የነጻነት ትግሎች እንዲቀጣጠሉ አድርጓል። በተለይም ከ20ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ ለነበሩ እንቅስቃሴዎች ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ይህ ታሪካዊ ዐሻራ ኢትዮጵያን የጥቁሮች ኩራት፣ ትግል እና ራስን የመቻል ምልክት እንድትሆን አስችሏታል። የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና አዲስ አበባ የአፍሪካ ኅብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ ኢትዮጵያ የአኅጉሪቷ የዲፕሎማሲ ማዕከል ሆና እንድትቀጥል አስችሏል። እ.አ.አ በ1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ኅብረት) ታሪካዊ ምሥረታ የተካሄደው በኢትዮጵያ ነው። ኢትዮጵያ ከድርጅቱ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ይህም የአፍሪካ የጋራ የፖለቲካ ድምጽ እንድትሆን ምክንያት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሴኤ) እና ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ተቋማት የሚገኙባት ኢትዮጵያ፤ በዲፕሎማሲው ምክክር እና ውሳኔ ሰጪነት ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የበለጠ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ድምጽ ኢትዮጵያ በቅኝ አለመገዛቷ ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ሥር መስደድ ወሳኝ ነው። በፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ለአፍሪካ አንድነት እና የጋራ ምላሽ አጥብቃ ስትሞግትም ቆይታለች። በአፍሪካ ኅብረት እና በተለያዩ መድረኮች ኢትዮጵያ የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን መፈታት አለባቸው የሚለውን እሳቤ ለማስረጽ አበክራ እየሠራች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተኮር መፍትሔዎች ከቃላት ባለፈ በአኅጉራዊ የትሥሥር አጀንዳዎች፣ ሰላም እና ደኅንነት ማዕቀፎች እንዲሁም የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ፈተናዎች እንዲፈቱ ድጋፏን በመስጠት ቁርጠኝነቷን አሳይታለች። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነትንም በፍጥነት አጽድቃ ወደ ሥራ ማስገባቷ የዚሁ አንድ ማሳያ ነው። ሰላም ማስከበር እና ቀጣናዊ መረጋጋት ኢትዮጵያ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ስትራቴጂካዊ ሚና እየተወጣች ነው። በዚህም መሠረት ለተባበሩት መንግሥታት እና የአፍሪካ ኅብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማድረግ ከአፍሪካ ሀገራት ቀዳሚውን ድርሻ ትይዛለች።   ሶማሊያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ ግጭት ባለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ወታደሮቿን በመላክ ለሰላም እና ደኅንነት ያላትን ሚና በተግባር ገልጣ አሳይታለች። የተባበሩት መንግሥታትም ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር እየተወጣች ላለው ሚና ምሥጋናውን ማቅረቡ ይታወቃል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሀገራት ያሉ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የተወጣችው የእርቅ እና የዲፕሎማሲ ሚናም ተጠቃሽ ነው።   የኢኮኖሚ እድገት እና ቀጣናዊ ትሥሥር ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል በዋናነት ትጠቀሳለች። በ2017 ዓ.ም ማብቂያ የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በግንባታ ላይ የሚገኘው ኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከግዙፍ መሠረተ ልማትነታቸው ባለፈ ቀጣናዊ ትሥሥር በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሚና አላቸው። ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢነርጂ የስኅበት ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት የምትሸጠው ኢነርጂ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን የሚያሳልጥ ነው። የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መንገድን ጨምሮ የመንገድ መሠረተ ልማቶች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኢትዮጵያን የቀጣናዊ ትሥሥር ማዕከል እንድትሆን እያደረጓት ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት እየተከናወነ ያለው አረንጓዴ ዐሻራም፤ ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ትብብር እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተምሳሌት ማድረግ ችሏል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ አጀንዳ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ትገኛለች። የባህል እና የሥልጣኔ አስተዋጽዖ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ታሪክ፣ ቱባ ባህል እና ብዝኃነት መገለጫዋ ናቸው። የቋንቋ ብዝኃነት በአፍሪካ ውስጥ ገራገር የዲፕሎማሲ ኃይል (Soft Power) እንዲኖራት አስተዋጽዖ አድርጓል። የኢትዮጵያ የሀገርነት ታሪክ እና የሥልጣኔ ትርክት አፍሪካ ያሏትን ጥልቅ የታሪክ ሥሮች ይበልጥ አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የኢትዮጵያ ብዝኃ ማንነቶች፣ ሀገር በቀል ዕውቀቶች እና አስደማሚ የሥነ-ሕንጻ ሥራዎች በአፍሪካ ባህል እና ሥልጣኔ ውስጥ ያላቸው ሚና ትልቅ ነው። ኢትዮጵያ አሁንም በአፍሪካ አንድነት እና መረጋጋት ውስጥ እንደ ቁልፍ ምሰሶ ትታያለች። በአኅጉሪቱ ውስጥ ያላት ድርሻ በታሪክ ሥር የሰደደ እና አሁን ባለው ዘመን በዲፕሎማሲ፣ በሰላም ግንባታ እና ልማት ሥራ በግልጽ ጎልቶ ይታያል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የፖለቲካ መዲና እንዲሁም የአይበገሬነት እና የነጻነት ምልክት ናት። አፍሪካ አንድነቷን ለማረጋገጥ፣ የተረጋጋ አኅጉር ለመፍጠር እና በራስ ዐቅም ነገሮችን የመከወን ጉዞ ትልም ውስጥ የኢትዮጵያ ድርሻ ቁልፍ ነው።   39ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ “ዘላቂ የውኃ ኑረትና ንጽህና ሥርዓት፤ ለአጀንዳ 2063 ስኬት” በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬና ነገ በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። ጉባዔው ኢትዮጵያ አኅጉራዊ የፖለቲካ እና ዲፕሎማሲያዊ መድረክ መሆኗን ዳግም የምታሳይበት ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም