ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው አርባምንጭ ከተማ ድል ቀንቶታል
May 28, 2026 128
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ መቻልን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አሸናፊ ተገኝ እና ቴዎድሮስ በንቲ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ፈቱዲን ጀማል ለመቻል ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው አርባምንጭ ከተማ በ32 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት እያደረገ ባለው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በሊጉም ስድስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቻል በ53 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት የማጥበብ እድል አልተጠቀመበትም። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ ቀን ላይ በተደረጉ የ34ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 1፣ ሀዋሳ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።
ሀዋሳ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ድል ቀንቷቸዋል
May 28, 2026 199
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵ ፕሪሚየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል። በረከት ሳሙኤል በ61ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል። የሃዋሳ ከተማው የአማካይ ተጫዋች ያሬድ ብሩክ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ከ10 ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሃዋሳ ከተማ በ48 ነጥብ ደረጃውን ከሰባተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉም 12ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 12ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ቡና በ46 ነጥብ ከነበረበት አምስተኛ ደረጃ ወደ ስድስተኛ ዝቅ ብሏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 1 ረቷል። ብሩክ አለማየሁ እና ሀብታሙ ጉልላት የማሸነፊያ ጎሎቹን ከመረብ ጋር አገናኝተዋል። አስራት ቱንጆ የድሬዳዋ ከተማን ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል። በሊጉ 12ኛ ድሉን ያስመዘገበው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ46 ነጥብ ከነበረበት 10ኛ ደረጃ ወደ 7ኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር 13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ35 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት ስምንት የሊግ ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ምሽት 12 ሰዓት ላይ መቻል ከአርባምንጭ ከተማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በሐረሪ ክልል ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል
May 28, 2026 170
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን የክልሉ የግብርና ልማት ቢሮ አስታውቋል። የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ነስረዲን አህመድ እንደገለጹት በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ይተከላሉ። ከሚተከሉ ችግኞች ውስጥም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የፍራፍሬና የደን ችግኞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም ከ200 ሺህ በላይ የሚሆኑት ለእንስሳት መኖ የሚያገለግሉ ችግኞች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የችግኝ ጣቢያዎች እየተከናወነ በሚገኘው ስራም ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን አንስተዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር እስከ አሁን የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት የክልሉን የደን ሽፋን በማሳደግና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሻሻሉ መምጣታቸውንም ነው የተናገሩት።
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያካሄዱት የምርጫ ክርክር መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርግ ዕድል የፈጠረ ነው
May 28, 2026 314
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያካሄዱት የምርጫ ክርክር መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርግ ዕድል የፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ገለጹ። ቦርድ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር ማጠናቀቂያ እና የጥሞና ጊዜ ማብሰሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በምርጫው ዜጎች በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ ቦርድ አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ እንዲካሄድ ተደርጓል። ቦርዱ በክርክር ዙሪያ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስልጠና መስጠቱን አመልክተው፤ ክርክሩ በገለልተኛ ባለሙያዎች እንዲመራ መደረጉን ጠቁመዋል። በምርጫ ክርክር ሂደቱ የሚነሱ ሃሳቦች እውነታን ለማረጋገጥ ሀቅ የሚያጠራ (ፋክት ቼክ) የሚያደርጉ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ መደረጉንም ተናግረዋል። በምርጫ ክርክሩ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሀሳቦቻቸውንና ፕሮግራሞቻቸውን ማቅረባቸውን ጠቁመው፤ የምርጫ ክርክር መድረኩ መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። ክርክሩ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ አስተዋጽኦ ላደረጉ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት እና ባለሙያዎች፣ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ በበኩላቸው፤ የምርጫ ክርክሩ ዲሞክራሲያዊ በሆነ እና የገለልተኝነት መርህን ጠብቆ መካሄዱን አስረድተዋል። የምጫ ክርክሩ በ19 ዙር መካሄዱን ጠቁመው፤ ክርክሩም በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ዲጂታል አማራጮች ለመራጩ ህዝብ ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። የክርክር መድረኩ ለቀጣይም ግብዓት የሚሆን እውቀት እና ልምድ የተገኘበት መሆኑን ነው ምክትል ሰብሳቢው የጠቆሙት።
የመስኖ ግድቦች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ እያፋጠኑ ነው
May 28, 2026 277
ነገሌ ቦረና፣ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦በምሥራቅ ቦረና ዞን አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ ግድቦች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ እያፋጠኑ መሆኑን የዞኑ መስኖና አርብቶ አደር ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የምሥራቅ ቦረና ዞን አብዛኛው ነዋሪ ሕይወትና መተዳደሪያው አርብቶ አደርነትና ከአነስተኛ የእርሻ ሥራ ጋር የተያያዘ ነው። አካባቢው በተደጋጋሚ ጊዜ በሚከሰት ድርቅና በተለዋዋጭ የአየር ንብረት መዛባት ምክንያት ከፍተኛ የሆነ የውኃ እጥረት ሲያጋጥመው ቆይቷል። ይህንን ለመፍታት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ትኩረት የተሰጠው አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት ላይ ነው። የመስኖ ግድቦቹ መገንባት ማኅበረሰቡ መደበኛውን የዝናብ ወቅትን ብቻ ከመጠበቅ ወጥቶ፣ ያለውን የከርሰ ምድርና የገፀ ምድር ውኃ በአግባቡ በመጠቀም በዓመት ሁለትና ሦስት ጊዜ እንዲያመርት ዕድል ፈጥሯል። የዞኑ መስኖና አርብቶ አደር ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው፤በዞኑ ቆላማ ወረዳዎች የተገነቡ ሁለት የመስኖ መሠረተ ልማቶች እየሰጡ ባለው አገልግሎት ዘርፈ ብዙ ጥቅም እያስገኙ ነው። በጽሕፈት ቤቱ የዲዛይንና ቁጥጥር ቡድን መሪ ኢንጂነር ተስፋሁነኝ ዳንኤል እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቶቹ በተለይም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚደረገው ሽግግር ውስጥ ትልቅ እገዛ እያደረጉ ነው። በተለይም በዞኑ በሊበንና በጎሮዶላ ወረዳዎች የተገነቡት ግድቦቹ ነዋሪውን ወደ መስኖ ልማት ማስገባት ያስቻሉ ሲሆን ለምርታማነት ዕድገትም አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው ብለዋል። እነዚህ የመስኖ ፕሮጀክቶች ከ8 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የዝናብ ውኃ የማጠራቀም አቅም እንዳላቸውም ገልጸዋል። የመስኖ ፕሮጀክቶቹ ከ465 ሄክታር በላይ መሬትን በዘመናዊ መስኖ ከማልማት ጎን ለጎን፣ የአካባቢውን የመኖና የውኃ ችግር የሚያቃልሉ መሆናቸውንም አስረድተዋል። በተጨማሪም ግድቦቹ ለአሳ ሀብት ልማትና ለቱሪዝም መዳረሻነት አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው የተገነቡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለአብነትም በዞኑ ድቤ አዳማ መስኖ ፕሮጀክት ግድብ ውስጥ እስካሁን ከ10 ሺህ በላይ የአሳ ጫጩቶች መለቀቃቸውን ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የዞኑ ነዋሪዎች እንዳሉት፥የመስኖ ፕሮጀክቶቹ በዘመናዊ መስኖ ልማት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ ያግዛቸዋል። በዞኑ ሊበን ወረዳ የሲሚንቆ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ቃሲም ገመዳ እንደገለጹት፤ አካባቢው በድርቅና በዝናብ እጥረት ሳቢያ በተደጋጋሚ የመኖና የውኃ ችግር ያጋጥመው ነበር። ቀደም ሲል መኖና ውኃ ፍለጋ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሲጋለጡ መቆየታቸውንም ያስታውሳሉ። በአካባቢያቸው በተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት የበጋ ስንዴን በዘመናዊ መስኖ በማልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም የእንስሳት መኖና የውኃ ችግርን ለማቃለል እንደሚያግዝ ጠቁመው፥የበጋ ስንዴ፣ ቲማቲም፣ድንችና ሽንኩርት በመስኖ ለማልማት ተዘጋጅተዋል። ሌላው ነዋሪ አቶ ጉዮ ጃተኒ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል መደበኛ ሥራቸውን ትተው የእንስሳት መኖና የመጠጥ ውኃ ፍለጋ ሩቅ መንገድ ይጓዙ እንደነበር ያስታውሳሉ። በአካባቢያቸው የተገነቡት የመስኖ ፕሮጀክቶች ከአካባቢያቸው ሳይርቁ የበጋ ስንዴ በማምረት ችግሩን በዘላቂነት ለመቋቋም እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያካሄዱት የምርጫ ክርክር መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርግ ዕድል የፈጠረ ነው
May 28, 2026 314
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያካሄዱት የምርጫ ክርክር መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርግ ዕድል የፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ገለጹ። ቦርድ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር ማጠናቀቂያ እና የጥሞና ጊዜ ማብሰሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በምርጫው ዜጎች በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ ቦርድ አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ እንዲካሄድ ተደርጓል። ቦርዱ በክርክር ዙሪያ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስልጠና መስጠቱን አመልክተው፤ ክርክሩ በገለልተኛ ባለሙያዎች እንዲመራ መደረጉን ጠቁመዋል። በምርጫ ክርክር ሂደቱ የሚነሱ ሃሳቦች እውነታን ለማረጋገጥ ሀቅ የሚያጠራ (ፋክት ቼክ) የሚያደርጉ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ መደረጉንም ተናግረዋል። በምርጫ ክርክሩ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሀሳቦቻቸውንና ፕሮግራሞቻቸውን ማቅረባቸውን ጠቁመው፤ የምርጫ ክርክር መድረኩ መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። ክርክሩ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ አስተዋጽኦ ላደረጉ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት እና ባለሙያዎች፣ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ በበኩላቸው፤ የምርጫ ክርክሩ ዲሞክራሲያዊ በሆነ እና የገለልተኝነት መርህን ጠብቆ መካሄዱን አስረድተዋል። የምጫ ክርክሩ በ19 ዙር መካሄዱን ጠቁመው፤ ክርክሩም በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ዲጂታል አማራጮች ለመራጩ ህዝብ ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። የክርክር መድረኩ ለቀጣይም ግብዓት የሚሆን እውቀት እና ልምድ የተገኘበት መሆኑን ነው ምክትል ሰብሳቢው የጠቆሙት።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታን በተመለከተ ባወጣው መረጃ
May 28, 2026 308
ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ 1. የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር አለበት፣ 2. የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣ 3. አግባብ ባለው አካል ሲጠየቅ መታወቂያውን ማሳየት አለበት፣ 4. የምርጫ ሕጉን ማክበር አለበት፣ 5. የምርጫውን ሂደት የመከታተል ተግባሩን ሲያከናውን መራጮች ማንን መምረጥ እንዳለባቸው አስተያየት ከመስጠት ወይም ተጽዕኖ ለማሳደር መሞከር የለበትም፣ 6. የምርጫ ቁሳቁሶችን መያዝ፥ ማንሳት፤ መነካካት ወይም በቁሳቁሶቹ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ተግባራትን መፈጸም የለበትም፣ 7. የምርጫ ጣቢያውን ኃላፊ ወይም ሠራተኛ ከማስፈራራት ወይም ሥራውን ከሚያደናቅፉ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣ 8. ወደ ድምፅ መስጫ ክፍሎች መግባት የለበትም፣ 9. ቦርዱ የሚያወጣውን የሥነ ምግባር ደንብ መፈረም እና ማክበር ይገባዋል፡፡ ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 121
ለምክክር ሂደቱ ውጤታማነት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው
May 28, 2026 408
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ውጤታማነት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እያበረከቱ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዋናው ሀገራዊ ጉባኤ ላይ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ለተባባሪ ባለድርሻ አካላት ቀርበው ግብዓት የማሰባሰብያ ውይይት እያካሄደ ይገኛል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ጊዜ፤ ኮሚሽኑ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ በስኬት መከናወኑን ገልፀው፤ ለምክክር ሂደቱ ውጤታማነት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። በምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ የተወከሉ በአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ ታላላቅ ህዝባዊ መድረኮች ላይ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ጠቁመው በዚህም በሁሉም ክልሎች፣ በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። የተቋማት እና ማህበራት፣ የወረዳ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የዳያስፖራ፣ የመንግስት ተቋማት እና በሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ከታቀደው አንጻር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ በስኬት ተከናውኗል ብለዋል። ይህም በቀጣይ ለሚካሄደው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ መሰረት መጣሉን ጨምረው ተናግረዋል። በሀገራዊ ምክክሩ ሂደት የአጀንዳ ቀረጻ ስራው በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል ሲሉም ዋና ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል። በኢትዮጵያ ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር ግዙፍ ተልዕኮ ተጥሎበት እየሰራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋናውን ሀገራዊ ጉባኤ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ኮሚሽኑ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎችና የህብረተሰብ ክፍሎች ሲያከናውናቸው የቆዩትን የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቶች በይፋ አጠቃሎ፣ አሁን ላይ የተለዩትን ዋና ዋና የሀገራዊ ጉባኤ አጀንዳዎች ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ማቅረብና ተጨማሪ ግብዓቶችን የመሰብሰብ ስራ ላይ መሆኑንም ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት እየተከናወነ ባለው በዚህ አዲስ ምዕራፍ፣ ኮሚሽኑ ያዘጋጃቸውንና ያደራጃቸውን የአጀንዳ ረቂቆች ለተባባሪ ባለድርሻ አካላት እያቀረበ ይገኛል ሲሉ ጠቁመዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ይህንን የግብዓት ማሰባሰብ ሂደት ካጠናቀቀ በኋላ፣ የተገኙትን አዳዲስ ሀሳቦች በማካተት ለመጨረሻውና ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አጀንዳ ይቀርባሉ ብለዋል። ይህ የተደራጀ አጀንዳ በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ ተወካዮች በሚሳተፉበትና ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ላይ ቀርቦ ምክክር እንደሚደረግበትም ጠቁመዋል። ኮሚሽኑ በቀጣይ ሀገራዊ ጉባኤውን ለመጥራት የምክክር አጀንዳዎችን መቅረጽና ተደራሽ ማድረግ የመሰሉ ስራዎች እንደሚከናወኑ አስታውቀዋል። በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ከአራት ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ምክክር የሚያደርጉ በመሆኑ ለዚህም ስኬት የሁሉም ድጋፍ ያስፈልጋል ነው ያሉት።
በጥሞና ወቅት ምን ምን ማድረግ አይቻልም?
May 28, 2026 551
ከዛሬ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ምርጫው ዕለት ድረስ ያሉት ቀናት የጥሞና ቀናት ናቸው። በነዚህ ቀናት ውስጥ መከናወን የሌለባቸው ጉዳዮች ፦ በአካልና በዐደባባይ የሚደረጉ ቅስቀሳዎች ማካሔድ አይቻልም ፖለቲካ ተኮር የሕዝብ ስብሰባዎችና ሠልፎች የቤት ለቤትና የዐደባባይ ላይ ቅስቀሳዎች አይካሔዱም ፤ የቅስቀሳ ኅትመቶችን እና ቁሳቁሶችን መለጠፍና ማሠራጨት እንዲሁም ለቅስቀሳ የሚያገለግሉ አልባሳትን መልበስም አይቻልም፤ በነዚህ የጥሞና ቀናት ውስጥም መገናኛ ብዙሃን ባሏቸው የተለያዩ የሚዲያ አውታሮች፣ ፕላትፎርሞች ማስተናገድ የሌለባቸው ጉዳዮች ፦ በቀጥታ ሥርጭትም ሆነ የተቀረጹ የዕጩ ወይም የፓርቲ ፕሮግራሞችን ማስተላለፍ አይቻልም፤ እነዚህ ስርጭቶች የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾችን በመጠቀም ቅስቀሳ ማድረግንም የሚያካትቱ በመሆናቸው አይስተናገዱም፤ በየትኛውም አካባቢ የፕሮጀክት ማስጀመር እና ማስመረቅ ሥራዎች በነዚህ የጥሞና ቀናት አይስተናገዱም የጥሞና ጊዜን ማክበር የምርጫውን ተዓማኒነት ያረጋግጣል! መራጩም ያለ ምንም ውጫዊ ተፅዕኖ፣ ግርግርና ቅስቀሳ በሰላም አስቦ እንዲወሥን ይረዳል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ አሸናፊነት የሚበሰርበት ነው
May 27, 2026 1174
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ድምፅ የኢትዮጵያ አሸናፊነት የሚበሰርበት መሆኑን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ። ድምፅ ከሚሰጥበት የጠቅላላ ምርጫ ዕለት አስቀድሞ የሚቀጥሉት አራት ቀናት የጥሞና ወቅት ሲሆኑ፤ በአካልና በአደባባይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችንና የመገናኛ ብዙኅን አጠቃቀምን ይገድባሉ። በዚህም በአካልና በአደባባይ የፖለቲካ ተኮር የህዝብ ስብሰባዎችና ሰልፎች፣ የቤት ለቤትና የአደባባይ እንቅስቃሴዎች፣ የቅስቀሳ ኅትመቶችንና ቁሳቁሶችን መለጠፍ እንዲሁም የቅስቀሳ አልባሳትን መልበስ በጥበቅ የተከለከሉ ተግባራት ናቸው። በመገናኛ ብዙኅን በቀጥታም ሆነ በተቀረጹ የዕጩዎች ወይም የፓርቲ ፕሮግራሞች ሥርጭት፣ የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾችን በመጠቀም ቅስቀሳ ማድረግ፣ ፕሮጀክት ማስጀመርና ማስመረቅ እንዲሁም በምርጫ ቦርድ መመሪያዎች ላይ ያልተደነገጉ ምርጫ ተኮር ተግባራትን መፈፀም በጥብቅ ተከልክሏል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሰሞኑ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫም ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ሁሉም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምክር ቤቱ የስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ልምድና ተሞክሮ በመቀመር ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት እየሰራ ነው። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅድመ ዝግጅትና የዲጂታል ዕጩዎች ምዝገባ ሂደት በስኬት ምዕራፍ ማጠናቀቅ እንደተቻለ ገልጸዋል። በዚህም የምክር ቤቱ አባል የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃ የአየር ሰዓት የፖሊሲ አማራጭ ማቀረባቸውን አመልክተው፤ በተለያዩ አካላት በተዘጋጁ የክርክር መድረኮች የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በፍትሐዊነት ለህዝብ ሃሳባቸውን ማስተዋወቅ መቻላቸውንም ተናግረዋል። የምርጫ ተከታታይ ኮሚቴ በማቋቋም ከምርጫ ቦርድ ጋር በመሆን ለጠቅላላ ምርጫ ሂደቱ አስቻይ ሁኔታዎችን ለማጥናትና ለመለየት ትልቅ ዕድል መፍጠሩንም አንስተዋል። ይህ የምርጫ ጉዳዮችን የሚከታተል ዴስክ አጠቃላይ ሁኔታዎችን በመገምገም፣ ስኬታማ ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን በቅርበት መከታተሉን አስታውቀዋል። ከግንቦት 20 ጀምሮ የጥሞና ጊዜ በመሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለምርጫ ሕጉ ተገዢ በመሆን ለዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት በአርዓያነት እንዲሰሩም አሳስበዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫው ኢትዮጵያ የምታሸንፍበት መሆኑንም ጨምረው አብራርተዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ላይ መራጩ ሕዝብ እንደተለመደው ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያረጋግጥ ጥሪ አቅርበዋል።
በጠቅላላ ምርጫው ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - የነቀምቴ ከተማ ነዋሪዎች
May 27, 2026 583
ነቀምቴ፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገርን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የነቀምቴ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ በምርጫው ለሀገር የሚበጅ፣ የተጀመሩ የልማትና የእድገት ጉዞዎችን የሚያስቀጥል እንዲሁም የሀገሪቱን አንድነት የሚያስጠብቅ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ነው የገለጹት። የነቀምቴ ከተማ ነዋሪው መንገሻ አከዩ፤ በሚዲያ ተቋማት በሚተላለፉ የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳዎች አማካኝነት በቂ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ምርጫ በመንግሥትና በህብረተሰቡ መካከል መግባባትን ከሚፈጥሩ ዋና ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም ህብረተሰቡ ይበጀኛል ያለውን አካል እንዲመርጥ እድል የሚሰጥ በመሆኑ ለሀገር ሰላም፣ አንድነትና እኩልነት የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ መስታወት ብርሃኑ በበኩላቸው፤ በመጪው ሀገራዊ ምርጫ በነፃነት ያመኑበትን ፓርቲ ለመምረጥና ድምፃቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። ከተለያዩ አካላት በተሰጡ የግንዛቤ ማስጨበጫዎች የፓርቲዎችን ምልክት ለይተው ማወቅ መቻላቸውንና ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸው፣ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም አክለው ተናግረዋል። በተመሳሳይ ሌላኛው ነዋሪ ምስጋኑ ጣሶ፤ በምርጫው ወቅት የሚጠበቅባቸውን የዜግነት ግዴታ ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸው፣ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም እና ልማት ይበጃል ያሉትን ፓርቲ እንደሚመርጡ አስታውቀዋል።
በምርጫ ክርክሩና በቅስቀሳው የፖሊሲና የስትራቴጂ አማራጮቻችንን ለህዝቡ በሚገባ አቅርበናል - የፖለቲካ ፓርቲዎች
May 27, 2026 689
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምርጫ ክርክሩና የቅስቀሳ መድረኮቹ የፖሊሲና የስትራቴጂ አማራጮቻቸውን ለህዝቡ በሚገባ ለማስተዋወቅ ሰፊ ዕድል እንደፈጠሩላቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስታወቀ ሲሆን፣ ከ50 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን አመልክቷል። ከግንቦት 20 እስከ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ማንኛውም ዓይነት የምርጫ ቅስቀሳ የማይደረግበት የጥሞና ጊዜ ነው። የተወዳዳሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቶዎቻቸውን ለህዝብ ሲያስተዋውቁና የምርጫ ክርክሮችን ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል። ይህንን ሂደት አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ በምርጫ ክርክሩና በቅስቀሳ መድረኮች ላይ የየራሳቸውን የፖሊሲና የስትራቴጂ አማራጮች ለህዝቡ በሚገባ ማቅረብ መቻላቸውን ገልጸዋል። የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀ መንበር እና የምርጫ ዴስክ አስተባባሪ አበራ በቀለ፤ ፓርቲያቸው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ዓላማ መግለጫ (ማኒፌስቶ) በማዘጋጀት ለህብረተሰቡ አቅርቦ ቅስቀሳ ማድረጉን ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ፓርቲው ያዘጋጃቸውን የተለያዩ የፖሊሲ አማራጮች እና የስትራቴጂ ማስፈጸሚያ ስልቶች ለህዝቡ በስፋት ማስተዋወቁን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የሰዓት ድልድል መሠረት፣ መገናኛ ብዙሃን የፖለቲካ ፓርቲዎች በክርክሮች ላይ የየራሳቸውን ሐሳብ እንዲያንሸራሽሩ በማመቻቸት በኩል ገንቢ ሚና መጫወታቸውንም አብራርተዋል። አሁን የተደረገውን የምርጫ ቅስቀሳ እና የተሰጠውን የመገናኛ ብዙሃን ሽፋን ከ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጋር ሲነጻጸር እጅግ የተሻለ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው በዕጩነት በሚወዳደርባቸው ዘጠኝ ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች ውስጥ የምርጫ ቅስቀሳዎችን በተከታታይ ሲያከናውን መቆየቱንም አስታውቀዋል። የፓርቲው አመራሮችና አባላት ቤት ለቤት በመዘዋወርና በራሪ ወረቀቶችን በማሰራጨት ባደረጉት የቅስቀሳ ሥራ ማከናወናቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሀገርን ማቀጠል የሚችል ጠንካራ እና ህጋዊ መንግስት መመስረት የሚችለው በምርጫና በምርጫ ብቻ መሆኑን ተገንዝቦ፣ ሂደቱ እንዲሳካ የበኩሉን አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበትም ገልጸዋል። ህዝቡ የእያንዳንዱን የምርጫ ካርድ ዋጋና ክብደት በሚገባ በመረዳት፣ በምርጫው ዕለት ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ እንዲመርጥም መልዕክት አስተላልፈዋል። በኢትዮጵያ ውስጥ ከምርጫ ውጪ ሌላ የፖለቲካ ሥልጣን ሽግግር መንገድ ሊኖር እንደማይገባ የገለጹት አቶ አበራ፤ በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ ዴሞክራሲያዊ ልምምድ እንዲዳብር የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አስገንዝበዋል። የህዳሴ ፓርቲ ፕሬዝዳንት የማነ አሰፋ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ጋር በመተባበር በመደበው የአየር ሰዓት በመጠቀም፣ የፖለቲካ ዓላማ መግለጫውን (ማኒፌስቶውን) እና አማራጭ ሐሳቦቹን በተለያዩ ሚዲያዎች ለህዝብ በሚገባ ማቅረቡን ገልጸዋል። ፓርቲው ያዘጋጃቸውን የፖሊሲና የሐሳብ አማራጮች ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ የተሻለ ሥራ ማከናወኑንም ጠቁመዋል። በተጨማሪም በራሪ ወረቀቶችን በማደል፣ ቤት ለቤት በመዘዋወርና የተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾችን (ሶሻል ሚዲያ) እንደ አማራጭ በመጠቀም ማኒፌስቶውንና ፖሊሲውን ሲያስተዋውቅ መቆየቱን ተናግረዋል። የህዳሴ ፓርቲ ከተለመደው የመወቃቀስ እና የብሽሽቅ ፖለቲካ አዙሪት ወጥቶ፣ በሐሳብ መሪነት ላይ የተመሠረተ የፖለቲካ እሳቤና በውይይት የሚያምን የፖለቲካ ባህልን እየተከተለ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ፓርቲያቸው በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የምርጫ ቅስቀሳዎችን ባደረገበት ወቅት ምንም ዓይነት የጸጥታም ሆነ የሌላ ችግር እንዳልገጠመውም ሊቀ መንበሩ ገልጸዋል። ለዚህም ሰላማዊ የቅስቀሳ ሂደት መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍ ላደረጉት የጸጥታ አካላት እና የመንግስት መዋቅሮች ምስጋና አቅርበዋል። በአጠቃላይ በምርጫ ክርክሩና በቅስቀሳው ወቅት ፓርቲዎች የየራሳቸውን ሐሳብ በነፃነት ማንሸራሸር መቻላቸው ለሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር መጎልበት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው አንስተዋል። በመጨረሻም ሊቀ መንበሩ ህዝቡ የተሰጠውን የምርጫ ካርድ በአግባቡ በመጠቀም ይበጀኛል፣ ያስተዳድረኛል የሚለውን ፓርቲ በነፃነት እንዲመርጥ ጥሪ አቅርበዋል።
ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ተገቢ ምላሽ ይሰጣል ለምንለው ፓርቲ ደምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል -የሃዋሳ ከተማና የዎንሾ ወረዳ ነዋሪዎች
May 27, 2026 529
ሃዋሳ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ተገቢ ምላሽ ይሰጣል ለሚሉት ፓርቲ ድምጻቸውን በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን በሲዳማ ክልል የሃዋሳ ከተማ እና የዎንሾ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ነዋሪዎቹ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በወቅቱ ወስደው የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ መሆናቸውንም ለኢዜአ ተናግረዋል። ግንቦት 24 ቀን በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ይሰጣል ለሚሉት ፓርቲ ድምጻቸውን በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙም ገልጸዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካካል የሃዋሳ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ጽጌ ይልማ የወሰዱትን ካርድ ተጠቅመው ለሀገርና ለሀዝብ የተሻለ አማራጭ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ እንደተዘጋጁ ተናግረዋል፡፡ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በቴክኖሎጂ ታግዞ የሚካሄድ መሆኑ ለየት ያደርገዋል ብለዋል። ለምርጫው የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያደረጉትን ቅስቀሳና የፖሊሲ አማራጭ በመገናኛ ብዙሀን መከታተላቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ አበራሽ ዋጄቦ ናቸው፡፡ በዚህም በድምጽ መስጫው ቀን ለህዝብ ዘርፈ ብዙ ጥያቄዎች ምላሽ ለሚሰጥ ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዕድሜያቸው ለመራጭነት የደረሱ ልጆቻቸው ጭምር ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ መውሰዳቸውን የሚናገሩት ደግሞ የዎንሾ ወረዳ ነዋሪ አቶ ባቢሶ ባራሞ ናቸው። በመጪው ሰኞ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ይሰጣል ለሚሉት ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት እንደተዘጋጁ ተናግረው፣ ዜጎች ካርዳቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙበት እየቀሰቀሱ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሌላው የዚሁ ወረዳ ነዋሪ መምህር ብርሃኑ ቢሊሶ በበኩላቸው የምርጫ ካርድ በወቅቱ ከመውሰድ ጀምሮ የፓርቲዎችን የክርክር መድረክ በአግባቡ መከታተላቸውን ተናግረዋል፡፡ ይህም ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመለየት እንዳስቻላቸው ገልጸው፤ ሀገርና ህዝብን በሰላምና ልማት ለሚያሻግር ፓርቲ ድምጼን ለመስጠት ተዘጋጅቼያለሁ ብለዋል።
ፖለቲካ
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያካሄዱት የምርጫ ክርክር መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርግ ዕድል የፈጠረ ነው
May 28, 2026 314
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያካሄዱት የምርጫ ክርክር መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርግ ዕድል የፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ገለጹ። ቦርድ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር ማጠናቀቂያ እና የጥሞና ጊዜ ማብሰሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በምርጫው ዜጎች በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ ቦርድ አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ እንዲካሄድ ተደርጓል። ቦርዱ በክርክር ዙሪያ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስልጠና መስጠቱን አመልክተው፤ ክርክሩ በገለልተኛ ባለሙያዎች እንዲመራ መደረጉን ጠቁመዋል። በምርጫ ክርክር ሂደቱ የሚነሱ ሃሳቦች እውነታን ለማረጋገጥ ሀቅ የሚያጠራ (ፋክት ቼክ) የሚያደርጉ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ መደረጉንም ተናግረዋል። በምርጫ ክርክሩ ፓርቲዎች የፖሊሲ ሀሳቦቻቸውንና ፕሮግራሞቻቸውን ማቅረባቸውን ጠቁመው፤ የምርጫ ክርክር መድረኩ መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። ክርክሩ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ አስተዋጽኦ ላደረጉ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት እና ባለሙያዎች፣ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ በበኩላቸው፤ የምርጫ ክርክሩ ዲሞክራሲያዊ በሆነ እና የገለልተኝነት መርህን ጠብቆ መካሄዱን አስረድተዋል። የምጫ ክርክሩ በ19 ዙር መካሄዱን ጠቁመው፤ ክርክሩም በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ዲጂታል አማራጮች ለመራጩ ህዝብ ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። የክርክር መድረኩ ለቀጣይም ግብዓት የሚሆን እውቀት እና ልምድ የተገኘበት መሆኑን ነው ምክትል ሰብሳቢው የጠቆሙት።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታን በተመለከተ ባወጣው መረጃ
May 28, 2026 308
ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ 1. የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር አለበት፣ 2. የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣ 3. አግባብ ባለው አካል ሲጠየቅ መታወቂያውን ማሳየት አለበት፣ 4. የምርጫ ሕጉን ማክበር አለበት፣ 5. የምርጫውን ሂደት የመከታተል ተግባሩን ሲያከናውን መራጮች ማንን መምረጥ እንዳለባቸው አስተያየት ከመስጠት ወይም ተጽዕኖ ለማሳደር መሞከር የለበትም፣ 6. የምርጫ ቁሳቁሶችን መያዝ፥ ማንሳት፤ መነካካት ወይም በቁሳቁሶቹ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ተግባራትን መፈጸም የለበትም፣ 7. የምርጫ ጣቢያውን ኃላፊ ወይም ሠራተኛ ከማስፈራራት ወይም ሥራውን ከሚያደናቅፉ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣ 8. ወደ ድምፅ መስጫ ክፍሎች መግባት የለበትም፣ 9. ቦርዱ የሚያወጣውን የሥነ ምግባር ደንብ መፈረም እና ማክበር ይገባዋል፡፡ ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 121
ለምክክር ሂደቱ ውጤታማነት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው
May 28, 2026 408
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ውጤታማነት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እያበረከቱ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዋናው ሀገራዊ ጉባኤ ላይ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ለተባባሪ ባለድርሻ አካላት ቀርበው ግብዓት የማሰባሰብያ ውይይት እያካሄደ ይገኛል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ጊዜ፤ ኮሚሽኑ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ በስኬት መከናወኑን ገልፀው፤ ለምክክር ሂደቱ ውጤታማነት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። በምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ የተወከሉ በአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ ታላላቅ ህዝባዊ መድረኮች ላይ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ጠቁመው በዚህም በሁሉም ክልሎች፣ በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። የተቋማት እና ማህበራት፣ የወረዳ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የዳያስፖራ፣ የመንግስት ተቋማት እና በሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ከታቀደው አንጻር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ በስኬት ተከናውኗል ብለዋል። ይህም በቀጣይ ለሚካሄደው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ መሰረት መጣሉን ጨምረው ተናግረዋል። በሀገራዊ ምክክሩ ሂደት የአጀንዳ ቀረጻ ስራው በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል ሲሉም ዋና ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል። በኢትዮጵያ ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር ግዙፍ ተልዕኮ ተጥሎበት እየሰራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋናውን ሀገራዊ ጉባኤ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ኮሚሽኑ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎችና የህብረተሰብ ክፍሎች ሲያከናውናቸው የቆዩትን የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቶች በይፋ አጠቃሎ፣ አሁን ላይ የተለዩትን ዋና ዋና የሀገራዊ ጉባኤ አጀንዳዎች ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ማቅረብና ተጨማሪ ግብዓቶችን የመሰብሰብ ስራ ላይ መሆኑንም ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት እየተከናወነ ባለው በዚህ አዲስ ምዕራፍ፣ ኮሚሽኑ ያዘጋጃቸውንና ያደራጃቸውን የአጀንዳ ረቂቆች ለተባባሪ ባለድርሻ አካላት እያቀረበ ይገኛል ሲሉ ጠቁመዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ይህንን የግብዓት ማሰባሰብ ሂደት ካጠናቀቀ በኋላ፣ የተገኙትን አዳዲስ ሀሳቦች በማካተት ለመጨረሻውና ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አጀንዳ ይቀርባሉ ብለዋል። ይህ የተደራጀ አጀንዳ በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ ተወካዮች በሚሳተፉበትና ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ላይ ቀርቦ ምክክር እንደሚደረግበትም ጠቁመዋል። ኮሚሽኑ በቀጣይ ሀገራዊ ጉባኤውን ለመጥራት የምክክር አጀንዳዎችን መቅረጽና ተደራሽ ማድረግ የመሰሉ ስራዎች እንደሚከናወኑ አስታውቀዋል። በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ከአራት ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ምክክር የሚያደርጉ በመሆኑ ለዚህም ስኬት የሁሉም ድጋፍ ያስፈልጋል ነው ያሉት።
በጥሞና ወቅት ምን ምን ማድረግ አይቻልም?
May 28, 2026 551
ከዛሬ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ምርጫው ዕለት ድረስ ያሉት ቀናት የጥሞና ቀናት ናቸው። በነዚህ ቀናት ውስጥ መከናወን የሌለባቸው ጉዳዮች ፦ በአካልና በዐደባባይ የሚደረጉ ቅስቀሳዎች ማካሔድ አይቻልም ፖለቲካ ተኮር የሕዝብ ስብሰባዎችና ሠልፎች የቤት ለቤትና የዐደባባይ ላይ ቅስቀሳዎች አይካሔዱም ፤ የቅስቀሳ ኅትመቶችን እና ቁሳቁሶችን መለጠፍና ማሠራጨት እንዲሁም ለቅስቀሳ የሚያገለግሉ አልባሳትን መልበስም አይቻልም፤ በነዚህ የጥሞና ቀናት ውስጥም መገናኛ ብዙሃን ባሏቸው የተለያዩ የሚዲያ አውታሮች፣ ፕላትፎርሞች ማስተናገድ የሌለባቸው ጉዳዮች ፦ በቀጥታ ሥርጭትም ሆነ የተቀረጹ የዕጩ ወይም የፓርቲ ፕሮግራሞችን ማስተላለፍ አይቻልም፤ እነዚህ ስርጭቶች የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾችን በመጠቀም ቅስቀሳ ማድረግንም የሚያካትቱ በመሆናቸው አይስተናገዱም፤ በየትኛውም አካባቢ የፕሮጀክት ማስጀመር እና ማስመረቅ ሥራዎች በነዚህ የጥሞና ቀናት አይስተናገዱም የጥሞና ጊዜን ማክበር የምርጫውን ተዓማኒነት ያረጋግጣል! መራጩም ያለ ምንም ውጫዊ ተፅዕኖ፣ ግርግርና ቅስቀሳ በሰላም አስቦ እንዲወሥን ይረዳል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ አሸናፊነት የሚበሰርበት ነው
May 27, 2026 1174
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ድምፅ የኢትዮጵያ አሸናፊነት የሚበሰርበት መሆኑን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ። ድምፅ ከሚሰጥበት የጠቅላላ ምርጫ ዕለት አስቀድሞ የሚቀጥሉት አራት ቀናት የጥሞና ወቅት ሲሆኑ፤ በአካልና በአደባባይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችንና የመገናኛ ብዙኅን አጠቃቀምን ይገድባሉ። በዚህም በአካልና በአደባባይ የፖለቲካ ተኮር የህዝብ ስብሰባዎችና ሰልፎች፣ የቤት ለቤትና የአደባባይ እንቅስቃሴዎች፣ የቅስቀሳ ኅትመቶችንና ቁሳቁሶችን መለጠፍ እንዲሁም የቅስቀሳ አልባሳትን መልበስ በጥበቅ የተከለከሉ ተግባራት ናቸው። በመገናኛ ብዙኅን በቀጥታም ሆነ በተቀረጹ የዕጩዎች ወይም የፓርቲ ፕሮግራሞች ሥርጭት፣ የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾችን በመጠቀም ቅስቀሳ ማድረግ፣ ፕሮጀክት ማስጀመርና ማስመረቅ እንዲሁም በምርጫ ቦርድ መመሪያዎች ላይ ያልተደነገጉ ምርጫ ተኮር ተግባራትን መፈፀም በጥብቅ ተከልክሏል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሰሞኑ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫም ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ሁሉም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምክር ቤቱ የስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ልምድና ተሞክሮ በመቀመር ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት እየሰራ ነው። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅድመ ዝግጅትና የዲጂታል ዕጩዎች ምዝገባ ሂደት በስኬት ምዕራፍ ማጠናቀቅ እንደተቻለ ገልጸዋል። በዚህም የምክር ቤቱ አባል የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃ የአየር ሰዓት የፖሊሲ አማራጭ ማቀረባቸውን አመልክተው፤ በተለያዩ አካላት በተዘጋጁ የክርክር መድረኮች የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በፍትሐዊነት ለህዝብ ሃሳባቸውን ማስተዋወቅ መቻላቸውንም ተናግረዋል። የምርጫ ተከታታይ ኮሚቴ በማቋቋም ከምርጫ ቦርድ ጋር በመሆን ለጠቅላላ ምርጫ ሂደቱ አስቻይ ሁኔታዎችን ለማጥናትና ለመለየት ትልቅ ዕድል መፍጠሩንም አንስተዋል። ይህ የምርጫ ጉዳዮችን የሚከታተል ዴስክ አጠቃላይ ሁኔታዎችን በመገምገም፣ ስኬታማ ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን በቅርበት መከታተሉን አስታውቀዋል። ከግንቦት 20 ጀምሮ የጥሞና ጊዜ በመሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለምርጫ ሕጉ ተገዢ በመሆን ለዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት በአርዓያነት እንዲሰሩም አሳስበዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫው ኢትዮጵያ የምታሸንፍበት መሆኑንም ጨምረው አብራርተዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ላይ መራጩ ሕዝብ እንደተለመደው ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያረጋግጥ ጥሪ አቅርበዋል።
በጠቅላላ ምርጫው ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - የነቀምቴ ከተማ ነዋሪዎች
May 27, 2026 583
ነቀምቴ፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገርን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የነቀምቴ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ በምርጫው ለሀገር የሚበጅ፣ የተጀመሩ የልማትና የእድገት ጉዞዎችን የሚያስቀጥል እንዲሁም የሀገሪቱን አንድነት የሚያስጠብቅ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ነው የገለጹት። የነቀምቴ ከተማ ነዋሪው መንገሻ አከዩ፤ በሚዲያ ተቋማት በሚተላለፉ የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳዎች አማካኝነት በቂ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ምርጫ በመንግሥትና በህብረተሰቡ መካከል መግባባትን ከሚፈጥሩ ዋና ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም ህብረተሰቡ ይበጀኛል ያለውን አካል እንዲመርጥ እድል የሚሰጥ በመሆኑ ለሀገር ሰላም፣ አንድነትና እኩልነት የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ መስታወት ብርሃኑ በበኩላቸው፤ በመጪው ሀገራዊ ምርጫ በነፃነት ያመኑበትን ፓርቲ ለመምረጥና ድምፃቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። ከተለያዩ አካላት በተሰጡ የግንዛቤ ማስጨበጫዎች የፓርቲዎችን ምልክት ለይተው ማወቅ መቻላቸውንና ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸው፣ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም አክለው ተናግረዋል። በተመሳሳይ ሌላኛው ነዋሪ ምስጋኑ ጣሶ፤ በምርጫው ወቅት የሚጠበቅባቸውን የዜግነት ግዴታ ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸው፣ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም እና ልማት ይበጃል ያሉትን ፓርቲ እንደሚመርጡ አስታውቀዋል።
በምርጫ ክርክሩና በቅስቀሳው የፖሊሲና የስትራቴጂ አማራጮቻችንን ለህዝቡ በሚገባ አቅርበናል - የፖለቲካ ፓርቲዎች
May 27, 2026 689
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምርጫ ክርክሩና የቅስቀሳ መድረኮቹ የፖሊሲና የስትራቴጂ አማራጮቻቸውን ለህዝቡ በሚገባ ለማስተዋወቅ ሰፊ ዕድል እንደፈጠሩላቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስታወቀ ሲሆን፣ ከ50 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን አመልክቷል። ከግንቦት 20 እስከ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ማንኛውም ዓይነት የምርጫ ቅስቀሳ የማይደረግበት የጥሞና ጊዜ ነው። የተወዳዳሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቶዎቻቸውን ለህዝብ ሲያስተዋውቁና የምርጫ ክርክሮችን ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል። ይህንን ሂደት አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ በምርጫ ክርክሩና በቅስቀሳ መድረኮች ላይ የየራሳቸውን የፖሊሲና የስትራቴጂ አማራጮች ለህዝቡ በሚገባ ማቅረብ መቻላቸውን ገልጸዋል። የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀ መንበር እና የምርጫ ዴስክ አስተባባሪ አበራ በቀለ፤ ፓርቲያቸው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ዓላማ መግለጫ (ማኒፌስቶ) በማዘጋጀት ለህብረተሰቡ አቅርቦ ቅስቀሳ ማድረጉን ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ፓርቲው ያዘጋጃቸውን የተለያዩ የፖሊሲ አማራጮች እና የስትራቴጂ ማስፈጸሚያ ስልቶች ለህዝቡ በስፋት ማስተዋወቁን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የሰዓት ድልድል መሠረት፣ መገናኛ ብዙሃን የፖለቲካ ፓርቲዎች በክርክሮች ላይ የየራሳቸውን ሐሳብ እንዲያንሸራሽሩ በማመቻቸት በኩል ገንቢ ሚና መጫወታቸውንም አብራርተዋል። አሁን የተደረገውን የምርጫ ቅስቀሳ እና የተሰጠውን የመገናኛ ብዙሃን ሽፋን ከ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጋር ሲነጻጸር እጅግ የተሻለ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲው በዕጩነት በሚወዳደርባቸው ዘጠኝ ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች ውስጥ የምርጫ ቅስቀሳዎችን በተከታታይ ሲያከናውን መቆየቱንም አስታውቀዋል። የፓርቲው አመራሮችና አባላት ቤት ለቤት በመዘዋወርና በራሪ ወረቀቶችን በማሰራጨት ባደረጉት የቅስቀሳ ሥራ ማከናወናቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሀገርን ማቀጠል የሚችል ጠንካራ እና ህጋዊ መንግስት መመስረት የሚችለው በምርጫና በምርጫ ብቻ መሆኑን ተገንዝቦ፣ ሂደቱ እንዲሳካ የበኩሉን አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበትም ገልጸዋል። ህዝቡ የእያንዳንዱን የምርጫ ካርድ ዋጋና ክብደት በሚገባ በመረዳት፣ በምርጫው ዕለት ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ እንዲመርጥም መልዕክት አስተላልፈዋል። በኢትዮጵያ ውስጥ ከምርጫ ውጪ ሌላ የፖለቲካ ሥልጣን ሽግግር መንገድ ሊኖር እንደማይገባ የገለጹት አቶ አበራ፤ በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ ዴሞክራሲያዊ ልምምድ እንዲዳብር የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አስገንዝበዋል። የህዳሴ ፓርቲ ፕሬዝዳንት የማነ አሰፋ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ጋር በመተባበር በመደበው የአየር ሰዓት በመጠቀም፣ የፖለቲካ ዓላማ መግለጫውን (ማኒፌስቶውን) እና አማራጭ ሐሳቦቹን በተለያዩ ሚዲያዎች ለህዝብ በሚገባ ማቅረቡን ገልጸዋል። ፓርቲው ያዘጋጃቸውን የፖሊሲና የሐሳብ አማራጮች ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ የተሻለ ሥራ ማከናወኑንም ጠቁመዋል። በተጨማሪም በራሪ ወረቀቶችን በማደል፣ ቤት ለቤት በመዘዋወርና የተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾችን (ሶሻል ሚዲያ) እንደ አማራጭ በመጠቀም ማኒፌስቶውንና ፖሊሲውን ሲያስተዋውቅ መቆየቱን ተናግረዋል። የህዳሴ ፓርቲ ከተለመደው የመወቃቀስ እና የብሽሽቅ ፖለቲካ አዙሪት ወጥቶ፣ በሐሳብ መሪነት ላይ የተመሠረተ የፖለቲካ እሳቤና በውይይት የሚያምን የፖለቲካ ባህልን እየተከተለ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ፓርቲያቸው በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የምርጫ ቅስቀሳዎችን ባደረገበት ወቅት ምንም ዓይነት የጸጥታም ሆነ የሌላ ችግር እንዳልገጠመውም ሊቀ መንበሩ ገልጸዋል። ለዚህም ሰላማዊ የቅስቀሳ ሂደት መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍ ላደረጉት የጸጥታ አካላት እና የመንግስት መዋቅሮች ምስጋና አቅርበዋል። በአጠቃላይ በምርጫ ክርክሩና በቅስቀሳው ወቅት ፓርቲዎች የየራሳቸውን ሐሳብ በነፃነት ማንሸራሸር መቻላቸው ለሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር መጎልበት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው አንስተዋል። በመጨረሻም ሊቀ መንበሩ ህዝቡ የተሰጠውን የምርጫ ካርድ በአግባቡ በመጠቀም ይበጀኛል፣ ያስተዳድረኛል የሚለውን ፓርቲ በነፃነት እንዲመርጥ ጥሪ አቅርበዋል።
ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ተገቢ ምላሽ ይሰጣል ለምንለው ፓርቲ ደምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል -የሃዋሳ ከተማና የዎንሾ ወረዳ ነዋሪዎች
May 27, 2026 529
ሃዋሳ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ተገቢ ምላሽ ይሰጣል ለሚሉት ፓርቲ ድምጻቸውን በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን በሲዳማ ክልል የሃዋሳ ከተማ እና የዎንሾ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ነዋሪዎቹ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በወቅቱ ወስደው የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ መሆናቸውንም ለኢዜአ ተናግረዋል። ግንቦት 24 ቀን በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ይሰጣል ለሚሉት ፓርቲ ድምጻቸውን በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙም ገልጸዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካካል የሃዋሳ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ጽጌ ይልማ የወሰዱትን ካርድ ተጠቅመው ለሀገርና ለሀዝብ የተሻለ አማራጭ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ እንደተዘጋጁ ተናግረዋል፡፡ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በቴክኖሎጂ ታግዞ የሚካሄድ መሆኑ ለየት ያደርገዋል ብለዋል። ለምርጫው የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያደረጉትን ቅስቀሳና የፖሊሲ አማራጭ በመገናኛ ብዙሀን መከታተላቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ አበራሽ ዋጄቦ ናቸው፡፡ በዚህም በድምጽ መስጫው ቀን ለህዝብ ዘርፈ ብዙ ጥያቄዎች ምላሽ ለሚሰጥ ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዕድሜያቸው ለመራጭነት የደረሱ ልጆቻቸው ጭምር ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ መውሰዳቸውን የሚናገሩት ደግሞ የዎንሾ ወረዳ ነዋሪ አቶ ባቢሶ ባራሞ ናቸው። በመጪው ሰኞ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ይሰጣል ለሚሉት ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት እንደተዘጋጁ ተናግረው፣ ዜጎች ካርዳቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙበት እየቀሰቀሱ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሌላው የዚሁ ወረዳ ነዋሪ መምህር ብርሃኑ ቢሊሶ በበኩላቸው የምርጫ ካርድ በወቅቱ ከመውሰድ ጀምሮ የፓርቲዎችን የክርክር መድረክ በአግባቡ መከታተላቸውን ተናግረዋል፡፡ ይህም ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመለየት እንዳስቻላቸው ገልጸው፤ ሀገርና ህዝብን በሰላምና ልማት ለሚያሻግር ፓርቲ ድምጼን ለመስጠት ተዘጋጅቼያለሁ ብለዋል።
ማህበራዊ
የኮሌራና የወባ በሽታዎችን ለመከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው
May 28, 2026 226
ባህር ዳር፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በክረምት መግቢያና መውጫ ወቅት የሚከሰቱ የኮሌራና የወባ በሽታዎችን መከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር በላይ በዛብህ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኢንስቲትዩቱ የሚከሰቱ በሽታዎችን ቀድሞ በመከላከል ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል። የሚስተዋሉ የጤና ስጋቶችን ቀድሞ በመተንበይ፣ የዳሰሳ ጥናት በማድረግ፣ አስፈላጊውን የሰው ኃይል፣ የሕክምና ግብዓትና በጀት በመመደብ የመከላከል ስራውን ለማቀላጠፍ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የክረምቱን መግባት ተከትሎ እስከ ታኅሣሥ 30 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ የሚዘልቅ የወባና የኮሌራ በሽታዎች የቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ ዕቅድ በማዘጋጀት ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል። ያለፉ ዓመታት መረጃዎች የሚያሳዩት በክረምት መግቢያና መውጫ ወቅት በዝናብ ስርጭት መቆራረጥ ሳቢያ በየቦታው የሚታቆረው ውሃ ለኮሌራና ወባ በሽታዎች ስርጭት መስፋፋት መንስኤ መሆኑን ጠቁመዋል። ችግሩን ለመቅረፍም ሃብትን፣ የሰው ሃይልንና እውቀትን በማስተባበር የህብረተሰቡን ጤና በመጠበቅ በማምረት ስራው ላይ እንዲያተኩር የማድረግ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። የኮሌራ በሽታን ለመከላከል ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር የእቅዱ አካል ነው ብለዋል። የወባ ወረርሽኝን ለመግታት ባለፈው ዓመት የተጀመረውን "የአርብ ቀን እጆች" ንቅናቄን አጠናክሮ በማስቀጠል በየሳምንቱ ህዝቡ በነቂስ በመውጣት ውሃ ያቆረ ቦታን በማፋሰስ ሌሎች የአካባቢ ቁጥጥር ተግባራትን ያከናውናል ነው ያሉት። እቅዱን ለማሳካትም በዞንና በወረዳ ከሚገኙ የጤና መዋቅሮችና የአደጋ ማስተባበሪያ ማዕከላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም ጠቅሰዋል።
ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን በአግባቡ መጠቀም እንዲችል ከጸጥታ አንጻር በቂ ዝግጅት ተድርጓል - የአማራ ክልል ፖሊስ
May 27, 2026 408
ባህር ዳር፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ህዝቡ በጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብቱን በአግባቡ መጠቀም እንዲችል ከጸጥታ አንጻር በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊነት የተደረጉ ዝግጅቶችን አስመልክተው ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ በክልሉ በተቀናጀ አግባብ በተሰራው የሰላም ማስከበር ስራ ውጤት ተመዝግቧል። በተለይም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚያስችሉ፣ ፀጥታን የሚያጠናክሩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል። የክልሉ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ መብቱን በአግባቡ መጠቀም እንዲችል ከጸጥታ አንጻር በቂ ዝግጅት መደረጉንም አረጋግጠዋል። ህዝቡ ሰላምን የሚያጠናክር እንቅስቃሴን በቁርጠኝነት እያገዘና እየደገፈ እንደሆነም አስረድተዋል። የክልሉ ፖሊስ ከህብረተሰቡና ከሌሎች የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመሆን ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በያቤሎ ከተማ የሚገኘውን የቦረና ባሕል ማዕከል መረቁ
May 27, 2026 478
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19 /2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በያቤሎ ከተማ የሚገኘውን የቦረና ባሕል ማዕከል ዛሬ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምረቃው ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በ2013 ዓ.ም የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦለት የነበረውና ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የባህል ማዕከል፤ በመደመር መጽሐፍ ሽያጭ የተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል። የባሕል ማዕከሉ በ57.6 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ እንደሆነም ገልጸዋል። ማዕከሉ የገዳን ሥርዓት ለማሳየት በልዩ ሁኔታ ዲዛይን የተደረገ ሲሆን በአንድ ጊዜ እስከ 2000 ሰዎች ማስተናገድ አቅም ያለው የስብሰባ አዳራሽ እና የቅርስ ሙዚየምን አካቶ መገንባቱን አመልክተዋል። በተጨማሪም ማዕከሉ የቦረናን ህዝብ ባሕል፣ ታሪክ እና ፍልስፍና ለትውልድ የማሸጋገር ቁልፍ ሚና ይኖረዋልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የአዲስ አበባ ፖሊስን ተቋማዊ ጥንካሬና ክብር የሚያስጠብቅ ውጤታማ የሪፎርም እርምጃ እየተወሰደ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
May 27, 2026 421
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስን ተቋማዊ ጥንካሬና ክብር የሚያስጠብቅ ውጤታማ የሪፎርም እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ፖሊስ በ100 ቀናት ዕቅድ የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች አፈፃጸም ማጠቃለያ የግምገማ መድረክ በዓድዋ ድል መታሰቢያ አካሂዷል። በመድረኩ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል አስራት ዴኔሮ እንዲሁም የጠቅላይ መምሪያው ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ተገኝተዋል። ከንቲባ አዳነች በዚሁ ጊዜ፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ተልዕኮን በብቃት መወጣት የሚያስችል ውጤታማ የሪፎርም እርምጃ መወሰዱን አስታውሰዋል። በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ከተወሰደው ውጤታማ የለውጥ እርምጃ አንፃርም የአዲስ አበባ ፖሊስ ተልዕኮን በብቃት መወጣት የሚያስችል ሪፎርም እንደሚያስፈልገው ተናግረዋል። በዚህም የአዲስ አበባ ፖሊስን ተቋማዊ ጥንካሬና ክብር የሚያስጠብቅ ውጤታማ የሪፎርም እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተዋል። በተቋሙ የሪፎርም እርምጃ የሚደረገው ድጋፍና ክትትልም የሠራዊቱን ሎጀስቲክስ፣ ሞራልና ሙያዊ ሥነ-ምግባር በመገንባት ተልዕኮን በብቃት መወጣት የሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ 3ኛዋን ዓለምአቀፍ የዲፕሎማሲ ማዕከል ከተማ ሰላምና ደኅንነትን በማስጠበቅ በወንጀል መከላከልና የሕግ የበላይነትን በማስፈን የተጣለበትን ከፍተኛ ኃላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የፖሊስ ሠራዊትን የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለመፍታት የመጀመሪያው ምዕራፍ የመኖሪያ መንደር ግንባታ በመጪው ሰኔ ወር እንደሚጀመር አስታውቀዋል። በቀጣይም ፖሊስ በመዲናዋ ለሚከናወኑ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች የሚያበረክተውን ጉልህ አስተዋጽኦ የበለጠ በማላቅ ከከተማዋ ፈጣን ዕድገት ጋር አብሮ መጓዝ እንደሚገባው አስገንዝበዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ 118 ዓመታትን ያስቆጠረ ታሪክ ያለው አንጋፋ ተቋም መሆኑን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅትም የመዲናዋን ሰላምና ደኅንነት 24/7 በማስጠበቅ ግዳጁን በብቃት እየተወጣ መሆኑንም ተናግረዋል። የተቋሙ ሁለንተናዊ የሪፎርም እርምጃ ተቋማዊ ተልዕኮን በብቃት በመወጣት የሠራዊት አባላቱን ጥቅምና ክብር የሚያስጠብቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
የመስኖ ግድቦች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ እያፋጠኑ ነው
May 28, 2026 277
ነገሌ ቦረና፣ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦በምሥራቅ ቦረና ዞን አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ ግድቦች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ እያፋጠኑ መሆኑን የዞኑ መስኖና አርብቶ አደር ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የምሥራቅ ቦረና ዞን አብዛኛው ነዋሪ ሕይወትና መተዳደሪያው አርብቶ አደርነትና ከአነስተኛ የእርሻ ሥራ ጋር የተያያዘ ነው። አካባቢው በተደጋጋሚ ጊዜ በሚከሰት ድርቅና በተለዋዋጭ የአየር ንብረት መዛባት ምክንያት ከፍተኛ የሆነ የውኃ እጥረት ሲያጋጥመው ቆይቷል። ይህንን ለመፍታት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ትኩረት የተሰጠው አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት ላይ ነው። የመስኖ ግድቦቹ መገንባት ማኅበረሰቡ መደበኛውን የዝናብ ወቅትን ብቻ ከመጠበቅ ወጥቶ፣ ያለውን የከርሰ ምድርና የገፀ ምድር ውኃ በአግባቡ በመጠቀም በዓመት ሁለትና ሦስት ጊዜ እንዲያመርት ዕድል ፈጥሯል። የዞኑ መስኖና አርብቶ አደር ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው፤በዞኑ ቆላማ ወረዳዎች የተገነቡ ሁለት የመስኖ መሠረተ ልማቶች እየሰጡ ባለው አገልግሎት ዘርፈ ብዙ ጥቅም እያስገኙ ነው። በጽሕፈት ቤቱ የዲዛይንና ቁጥጥር ቡድን መሪ ኢንጂነር ተስፋሁነኝ ዳንኤል እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቶቹ በተለይም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚደረገው ሽግግር ውስጥ ትልቅ እገዛ እያደረጉ ነው። በተለይም በዞኑ በሊበንና በጎሮዶላ ወረዳዎች የተገነቡት ግድቦቹ ነዋሪውን ወደ መስኖ ልማት ማስገባት ያስቻሉ ሲሆን ለምርታማነት ዕድገትም አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው ብለዋል። እነዚህ የመስኖ ፕሮጀክቶች ከ8 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የዝናብ ውኃ የማጠራቀም አቅም እንዳላቸውም ገልጸዋል። የመስኖ ፕሮጀክቶቹ ከ465 ሄክታር በላይ መሬትን በዘመናዊ መስኖ ከማልማት ጎን ለጎን፣ የአካባቢውን የመኖና የውኃ ችግር የሚያቃልሉ መሆናቸውንም አስረድተዋል። በተጨማሪም ግድቦቹ ለአሳ ሀብት ልማትና ለቱሪዝም መዳረሻነት አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው የተገነቡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለአብነትም በዞኑ ድቤ አዳማ መስኖ ፕሮጀክት ግድብ ውስጥ እስካሁን ከ10 ሺህ በላይ የአሳ ጫጩቶች መለቀቃቸውን ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የዞኑ ነዋሪዎች እንዳሉት፥የመስኖ ፕሮጀክቶቹ በዘመናዊ መስኖ ልማት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ ያግዛቸዋል። በዞኑ ሊበን ወረዳ የሲሚንቆ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ቃሲም ገመዳ እንደገለጹት፤ አካባቢው በድርቅና በዝናብ እጥረት ሳቢያ በተደጋጋሚ የመኖና የውኃ ችግር ያጋጥመው ነበር። ቀደም ሲል መኖና ውኃ ፍለጋ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሲጋለጡ መቆየታቸውንም ያስታውሳሉ። በአካባቢያቸው በተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት የበጋ ስንዴን በዘመናዊ መስኖ በማልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም የእንስሳት መኖና የውኃ ችግርን ለማቃለል እንደሚያግዝ ጠቁመው፥የበጋ ስንዴ፣ ቲማቲም፣ድንችና ሽንኩርት በመስኖ ለማልማት ተዘጋጅተዋል። ሌላው ነዋሪ አቶ ጉዮ ጃተኒ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል መደበኛ ሥራቸውን ትተው የእንስሳት መኖና የመጠጥ ውኃ ፍለጋ ሩቅ መንገድ ይጓዙ እንደነበር ያስታውሳሉ። በአካባቢያቸው የተገነቡት የመስኖ ፕሮጀክቶች ከአካባቢያቸው ሳይርቁ የበጋ ስንዴ በማምረት ችግሩን በዘላቂነት ለመቋቋም እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።
በጂማ ከተማ የሥራ ዕድል የተመቻቸላቸው ወጣቶች ተጠቃሚነታቸው አድጓል
May 28, 2026 206
ጂማ፣ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በጂማ ከተማ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ወጣቶች ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገለጹ። በከተማዋ የወጣቶችን የሥራ ዕድል ለማስፋት የግብርና፣ የቴክኖሎጂና የንግድ ሥልጠናዎችን በመስጠት፣ የመሥሪያና መሸጫ ቦታዎችን በማቅረብ እንዲሁም የገበያ ትስስር በመፍጠር ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። በከተማዋ ኢዜአ ያነጋገረው ወጣት አብዱረሂም ናስር እንደገለጸው፤ የከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸለት የሥራ ዕድል በመጠቀም የዳቦ መጋገሪያ ማሽኖችን በጥራት አምርቶ ለገበያ እያቀረበ ይገኛል። እነዚህ ማሽኖች ከውጭ የሚገቡ የዳቦ መጋገሪያ ምርቶችን በመተካት የውጭ ምንዛሬን ከማዳናቸው ባለፈ፣ ኃይል ቆጣቢ በመሆናቸው በገበያ ላይ ተመራጭ መሆናቸውን አስረድቷል። ይህም ገቢውን ከመጨመር ባለፈ ለሌሎች ወጣቶች የሥራ ዕድል እንዲፈጥር እንዳገዘው ጠቁሟል። በተመሳሳይ ዘመናዊ ቦርሳዎችንና የቆዳ ውጤቶችን በማምረት ለገበያ እያቀረቡ ከሚገኙ ወጣቶች መካከል ደርሶልኝ ሽመልስ እና ሀብታሙ ጋዲሳ ይጠቀሳሉ። ወጣቶቹ እንደሚያስረዱት፤ የሚያመርቷቸው የቆዳ ውጤቶች በቅርጽም ሆነ በጥራት የሸማቹን ፍላጎት ያሟሉ በመሆናቸው በገበያ ላይ ተወዳዳሪ መሆን ችለዋል። ሥራቸውን ይበልጥ ለማስፋፋትም የከተማ አስተዳደሩ የብድርና የመሥሪያ ቦታ እንዳመቻቸላቸው ገልጸዋል። የጂማ ከተማ የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱልሀሚድ ኑረዲን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በከተማዋ ለወጣቶች የሥራ ዕድልን ለማስፋፋት በርካታ የመሥሪያና የመሸጫ ሼዶች ተገንብተዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ከ3 ሺህ በላይ በማኅበራት ለታቀፉ 20 ሺህ 160 ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ፣ ዕቅዱን በማሳለጥ 28 ሺህ 500 ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። የወጣቶቹን ስኬት ይበልጥ ለማገዝ የሥልጠናና የብድር አቅርቦት መመቻቸቱን የገለጹት ኃላፊው፤ በበጀት ዓመቱ እስካሁን 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት መቅረቡን ጠቁመዋል። ለወጣቶቹ የሥራ ዕድልን ለማስፋፋትም ለቡና መፈልፈያ፣ ለዳቦና እንጀራ መጋገሪያ፣ ለቆዳና እንጨት ሥራዎች እንዲሁም ለሌሎችም ተኪ ምርቶች ማምረቻ የሚሆኑ ሼዶች መሰጠታቸውን አክለዋል። ወደ ሥራ የገቡት ወጣቶች ምርቶቻቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለሕብረተሰቡ ከማቅረብ ባለፈ፣ ተኪ ምርቶችን በማምረት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻላቸውንም አቶ አብዱልሀሚድ ገልጸዋል።
በአማራ ክልል በዘንድሮው መኸር እርሻ ከ876 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በሰሊጥና አኩሪ አተር ይለማል
May 28, 2026 185
ባህርዳር ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዘንድሮው መኸር እርሻ ከ876ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ለኢንዱስትሪና ለውጭ ገበያ የሚውል የሰሊጥና የአኩሪ አተር እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ሰሊጥ ከቡና ቀጥሎ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከሚያስገኙ የግብርና ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ነው። አኩሪ አተርም ለምግብ ዘይት ፋብሪካዎችና ለእንስሳት መኖ ኢንዱስትሪዎች ወሳኝ ግብዓት ከመሆኑም በላይ፣ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያለው ተፈላጊነት እየጨመረ የመጣ ሰብል ነው። በአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት ለኢንዱስትሪና ለወጪ ምርት ግብዓት የሚውሉ ሰብሎችን በጥራትና በብዛት ለማምረት ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው። በዚህም በዘንድሮው የመኸር እርሻ የአየር ንበረታቸውና ስነ ምህዳራቸው ተስማሚ በሆኑ አካባቢዎች የሰሊጥና አኩሪ አተር ሰብሎች በስፋት ለማልማት ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል። በዚህም በክልሉ ከሚለማው 876ሺህ 870 ሄክታር መሬት፤ 463ሺህ 566 ሄክታር በሰሊጥ ቀሪው ደግሞ በአኩሪ አተር እንደሚለማ ተናግረዋል። ከልማቱ ከ15 ነጥብ 3 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ጠቁመው የዘር ወቅት በመድረሱም ዘርና ማዳበሪያ እየቀረበ ነው ብለዋል።
ባሕር ዳር ለነዋሪዎቿ ምቹ ለዓለምአቀፍ ጎብኚዎች ደግሞ ተመራጭ የቱሪስት ከተማ እየሆነች ነው - ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው
May 27, 2026 689
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ ባሕር ዳር በኮሪደር ልማት ለነዋሪዎቿ ምቹ ለዓለምአቀፍ ጎብኚዎች ደግሞ ተመራጭ የቱሪስት ከተማ እየሆነች ነው ሲሉ የባህርዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ። የባሕር ዳር ከተማን ውበትና ፅዳት በመጠበቅ ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ደግሞ ተመራጭና ረጅም ጊዜ የሚቆዩባት የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የተቀረጸው ዕቅድ በተግባር እየተተረጎመ ይገኛል። የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፣ ይህንን ግብ ለማሳካት የተቋቋመው የስማርት ባህርዳር ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት መሪነቱን በመውሰድ የኮሪደርና የጣና ዳርቻ ልማቶችን ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ፍጥነት እያከናወነ ነው። የከተማዋን ገጽታ የቀየሩ የጣና እና የዓባይ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋ ተፈጥሯዊ ሀብቶች የሆኑትን የጣና ሐይቅንና የዓባይ ወንዝን ለቱሪዝም ምቹ የማድረግ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶታል ነው ያሉት። በአሁኑ ወቅት በሐይቁ ዳርቻ ላይ ዘጠኝ የሚደርሱ ቦታዎች መልማታቸውን ጨምረው አስታውቀዋል። ይህም ከተማዋ፣ ነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከሐይቁ ጋር ያላቸውን መስተጋብር በእጅጉ አሳድጎታል ብለዋል። ከዚሁ ልማት ጋር ተያይዞም የዘንባባ ፓርክ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ የከተማዋን ውበት ይበልጥ እንዳደመቀው ገልጸዋል። የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ዋና ዋና መስመሮች እያደሰ ያለው የኮሪደር ልማት ከደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ እስከ ዓባይ ማዶ ባለው ዋና መንገድ ላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተገነባ ይገኛል ብለዋል። ይህ መሠረተ ልማት ከ5 እስከ 7 ሜትር የሚደርስ ሰፊ የእግረኛ መንገድ፣ እስከ 4 ሜትር ስፋት ያላቸው ውብ አረንጓዴ መናፈሻዎች፣ እስከ 3 ሜትር ስፋት ያለው የተለየ የብስክሌት መንገድ፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ የሕዝብ ማረፊያዎችና የሕፃናት መጫወቻዎች ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን እስከ ፓፒረስ ሆቴል ድረስ ያለው የእግረኛ መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝም አንስተዋል። በከተማዋ የዓባይ ወንዝን ዳርቻን ለማልማት መታቀዱንም ነው የጠቆሙት። የከተማዋ የኮሪደር ልማት ዕቅድ ሲቀረጽ ጀምሮ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ የፌደራል መንግሥቱ ፕሮጀክቱን በመገምገምና አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የላቀ የመሪነት ሚና መጫወታቸውንም አስረድተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ ተገኝተው የልማት ሥራዎቹን መገምገማቸውንና ለቀጣይ ተግባራት አቅጣጫ ማስቀመጣቸውንም ነው ያነሱት አቶ ጎሹ እንዳላማው። ለኮሪደር ልማቱ ስኬት የከተማዋ ነዋሪዎችና ባለሀብቶች በገንዘብና በሐሳብ እያደረጉት ያለው ተሳትፎ አይተኬ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። ከተማ አስተዳደሩ ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ መሰል የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አረጋግጠዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች
May 28, 2026 203
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ገለጹ። የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ መርሃ ግብር በዲጂታል ሳይንስ ዘርፎች እንደ አንድሮይድ ማበልጸግ፣ ዳታ አናሊቲክስ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዌብ ዲዛይን መሰረታዊ ስልጠናዎችን ያካተተ ነው። የመርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማና ግብ አምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በዲጂታል ክህሎት በማብቃት፣ ሀገሪቱ በዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ ያላትን ተወዳዳሪነት ማረጋገጥ ነው። ይህም ለወጣቶች ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያለው ሰርቲፊኬት እና የስራ ዕድሎችን በመፍጠር በኩል ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎቹ እንደገለጹት ከመደበኛው ትምህርት በተጨማሪ ራሳቸውን ከዲጂታሉ ዓለም ጋር ለማላመድ ጥረት እያደረጉ ነው። በለም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው አቢጊያ ዳንኤል፣ ወደፊት የሶፍትዌር ኢንጂነር የመሆን ህልሟን ለማሳካት በትምህርት ቤትና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመቻቹ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድሎችን እየተጠቀመች መሆኗን ገልጻለች። በዚሁ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አላዛር ማስሬ፣ በዲጂታል ዘርፍ ራሱን እያበቃ መሆኑን ገልጾ፤ ትውልዱ ነገ ተወዳዳሪ ዜጋ ለመሆን ራሱን ከቴክኖሎጂ ጋር ማላመድ የግድ መሆኑን ተናግሯል። በድልበር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አቤል ሙሉጌታ በበኩሉ፣ የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መውሰዱን ገልጾ፣ ተማሪዎች ከቴክኖሎጂ ጋር ለመራመድ የተፈጠረውን መልካም አጋጣሚ እንዲጠቀሙበት መክሯል። የዌብ ዲዛይን ስልጠና መውሰዱንና ይህም በዘርፉ ያለውን መሰረታዊ እውቀት እንዳስጨበጠው የተናገረው ደግሞ ተማሪ ፍራኦል ተሾመ ነው። የለም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ሰለሞን ዲሮ ትምህርት ቤቱ ከተለያዩ አካላት ጋር በመተባበር በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስና በሌሎች የቴክኖሎጂ ዘርፎች ለተማሪዎች ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የድልበር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር ተመስገን ቶሊና በበኩላቸው፣ ተማሪዎችና መምህራን የ5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ትምህርት ቤቱ ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል።
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው
May 28, 2026 243
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨርሲቲው 43ኛውን ዓመታዊ የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ግምገማ ጉባዔ ’’ለአካባቢ ተስማሚ ፈጠራና ስነ ምህዳር ጥበቃ ለጽኑ ማህበረሰብ ግንባታ’’ በሚል መሪ ሀሳብ እያካሄደ ነው። የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ይስሃቅ ዩስፍ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው በግብርና፣ በጤና፣ በቴክኖሎጂ፣ በትምህርት፣ በህግ፣ በህብረተሰብ ሳይንስና በሌሎችም የምርምር ተግባራት እያከናወነ ነው። በተለይም ዘንድሮ ዩኒቨርሲቲው 116 ፕሮጀክቶች ላይ የምርምር ስራ እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥም 42ቱ መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው ከ1 ቢሊየን ብር በላይ በጀት በመመደብ የሚያከናውናቸው የጥናትና ምርምር ቴክኖሎጂዎችም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ እንደሚገኙም አስታውቀዋል። ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮ ዓመትም ከ95 በላይ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ማሰራጨቱን አመልክተዋል። በዩኒቨርሲቲው ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና አስተዳደር ጋር በተያያዘ በድሬዳዋ አስተዳደር፣ በሐረማያ ሀይቅ፣ በአዴሌ፣ ደንጋጎ እና ሌሎች ተፋሰስ አካባቢዎች ላይ የተቀናጀ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። በማህበረሰብ አገልግሎትና ተሳትፎ በኩልም ከ150ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ነፃ የህግ አገልግሎት ከመስጠት በተጨማሪ በጤና፣ በትምህርትና በሌሎች ዘርፎች አመርቂ ተግባራት ማከናወኑን አንስተዋል። የግምገማ መድረኩ ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን አበረታች ስራዎች ለማስቀጠልና የሚስተዋሉ ውስንነቶች ለመቅረፍ እንደሚያስችል ተመላክቷል። ዩኒቨርሲቲው ለ43ኛ ጊዜ በሚያካሂደው የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ጉባዔ 32 የምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል። ለሶስት ቀናት በተሰናዳው በዚሁ ጉባዔ ላይ የዩኒቨርሲቲው ምሁራንና ተመራማሪዎች፣ ሴክተር መስሪያ ቤቶች፣ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የማህበረሰብ ተወካዮች፣ አባ ገዳዎችና ሃደ ሲንቄዎች እየተሳተፉ ነው።
በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት ለማሳደግ ተቋማት በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ እንዲደራጁ እየተደረገ ነው
May 26, 2026 793
አምቦ፤ ግንቦት 18/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት ለማሳደግ ተቋማት በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ እንዲደራጁ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ። በአምቦ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ፕሮጀክቶች ምረቃና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በገባው ቃል መሰረት በርካታ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በብዛት ገንብቶ ለአገልግሎት እያበቃ ይገኛል። በዚህም መሰረት በአምቦ ከተማ አስተዳደር ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ በርካታ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ አድርጓል። ከፕሮጀክቶቹ መካከል የአምቦ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና ለተለያዩ ቢሮዎች አገልግሎት የሚውል ባለ አምስት ወለል ህንፃ፣ በርካታ ሼዶችና ለሌሎች አገልግሎቶች የሚውሉ ግንባታዎች ተጠናቀው ተመርቀዋል። በወቅቱም የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ እንደገለፁት፤ በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ ተቋማት በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ እየተደራጁ ይገኛሉ ብለዋል። ለዚህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን የተገልጋይን እርካታ ለማሳደግ የማይተካ ድርሻ አለው ነው ያሉት። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ችግር በመፍታት ህብረተሰቡ ጊዜና ጉልበቱን በልማት ላይ እንዲያውል ተደማሪ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል። እንዲሁም የመንግሥት አገልግሎትን ከአድሎ የጸዳና ጥራት ያለው በማድረግ ብልሹ አሰራርን በማስወገድ በኩል ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በበኩላቸው፤ መንግሥት ከተሞችን ለኑሮና ለቱሪዝም ዘርፍ ተመራጭ ለማድረግ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን አንስተዋል። የአምቦ ከተማን የቱሪስት ማዕከል ለማድረግ የወንጪ-ዳንዲ-ኢኮቱሪዝም መንደር እና ሎጅ እንዲሁም ሌሎች ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በከተማዋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የአምቦ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሃጫሉ ገመቹ ናቸው፡፡ ዛሬ በከተማው ከተመረቀው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተጨማሪ ሼዶች፣ የከተማ ኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በከተማዋ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እንደሚያሳድጉም ጨምረው ተናግረዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ጠንካራ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ሥርዓት መገንባት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ ነው
May 26, 2026 463
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2018(ኢዜአ)፦ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ጠንካራ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ሥርዓት መገንባት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ገለጸ። የአእምሯዊ ንብረት ዘርፍ ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን ከሀገራዊ የአእምሯዊ ንብረት ምዝገባና ጥበቃ ጋር ማቀናጀት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሂዷል። የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ የግዙፍ ኩባንያዎች ሃብት ከፍተኛው ድርሻ ወደ አእምሯዊ ንብረት እየተቀየረ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያም የአእምሯዊ ንብረት ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የፖሊሲ፣ የሕግና የዲጂታል የአእምሯዊ ንብረት አስተዳደር ሥርዓት እየተዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል። የአእምሯዊ ንብረት ምዝገባ ሥርዓቱን በአስቻይ የአሰራር ምኅዳር ለሀገር የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የራሱን ድርሻ እንዲወጣ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከሀገር ውስጥና ዓለምአቀፍ ሕግና ስምምነቶች ጋር የተጣጣመ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት፣ ለጥናትና ምርምር ሥራ መሳለጥ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጥበቃ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነትና የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የንግድና ፈጠራ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ አይነተኛ ሚና እንደሚኖረው አንስተዋል። የአእምሯዊ ንብረት ዘርፍ የሕግ አማካሪ ኤልያስ ፍቅሩ፤ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ዓለምአቀፍ ፈጠራና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ወሳኝ ፋይዳ አለው ብለዋል። የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ሥርዓት መጠናከር ፈጠራና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የቅጂና ተዛማች መብቶች የጋራ አስተዳደር ማኅበር የቦርድ አባል አርቲስት ጸደንያ ገብረማርቆስ፤ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ የሚደረግላቸው ምርቶች ለኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ ፋይዳ አላቸው ብላለች። ለዚህም የኪነ-ጥበብ ሥራ ቅጂና ተዛማጅ የሕግ ግንዛቤን በማጎልበት ጠንካራ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ አቅም መገንባት እንደሚያስፈልግ ተናግራለች።
ስፖርት
በወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው አርባምንጭ ከተማ ድል ቀንቶታል
May 28, 2026 128
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ መቻልን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አሸናፊ ተገኝ እና ቴዎድሮስ በንቲ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ፈቱዲን ጀማል ለመቻል ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው አርባምንጭ ከተማ በ32 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት እያደረገ ባለው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በሊጉም ስድስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቻል በ53 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት የማጥበብ እድል አልተጠቀመበትም። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ ቀን ላይ በተደረጉ የ34ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 1፣ ሀዋሳ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።
ሀዋሳ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ድል ቀንቷቸዋል
May 28, 2026 199
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵ ፕሪሚየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል። በረከት ሳሙኤል በ61ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል። የሃዋሳ ከተማው የአማካይ ተጫዋች ያሬድ ብሩክ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ከ10 ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሃዋሳ ከተማ በ48 ነጥብ ደረጃውን ከሰባተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉም 12ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 12ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ቡና በ46 ነጥብ ከነበረበት አምስተኛ ደረጃ ወደ ስድስተኛ ዝቅ ብሏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 1 ረቷል። ብሩክ አለማየሁ እና ሀብታሙ ጉልላት የማሸነፊያ ጎሎቹን ከመረብ ጋር አገናኝተዋል። አስራት ቱንጆ የድሬዳዋ ከተማን ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል። በሊጉ 12ኛ ድሉን ያስመዘገበው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ46 ነጥብ ከነበረበት 10ኛ ደረጃ ወደ 7ኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር 13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ35 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት ስምንት የሊግ ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ምሽት 12 ሰዓት ላይ መቻል ከአርባምንጭ ከተማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ሉሲዎቹ ወደ ብሩንዲ አቀኑ
May 28, 2026 204
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን (ሉሲዎቹ)፣ ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታቸውን ከብሩንዲ አቻቸው ጋር ለማድረግ ወደ ስፍራው አቅንተዋል። ብሔራዊ ቡድኑ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ባደረገው ጨዋታ ብሩንዲን 2 ለ 1 አሸንፏል። ከጨዋታው መልስ ሉሲዎቹ የሀገር ቤት ዝግጅታቸውን ትናንት አጠናቀዋል። በአሰልጣኝ ራውዳ አሊ የሚመራው ይኸው ስብስብ ረፋድ ላይ ወደ ቡጁምቡራ ማቅናቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የሁለቱ ሀገራት የመልስ ጨዋታ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓም በኢንትዋሪ ስታዲየም ይካሄዳል። ኢትዮጵያ በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈች በመጨረሻው ዙር ማጣሪያ ከዛምቢያ እና ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
መቻል ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማጥበብ ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ይጫወታል
May 28, 2026 251
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከኢትዮጵያ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር በኋላ ዛሬ በ34ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ወደ ውድድር ይመለሳል። ከመርሐ ግብሮቹ መካከል ምሽት 12 ሰዓት ላይ መቻል እና አርባምንጭ ከተማን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታ ተጠቃሽ ነው። መቻል በ53 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። አርባምንጭ ከተማ በ29 ነጥብ የመጨረሻው 20ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ33ኛ ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር አንድ አቻ የተለያየው መቻል ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ ይጫወታል። መቻል ድል ከቀናት ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ያደርጋል። ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ከድል የራቀው አርባምንጭ ከተማ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት ያለውን ተስፋ ለማለምለም የግድ ሶስት ነጥብ ማግኘት ይጠበቅበታል። በሌላኛው መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ስታዲየም ይጫወታሉ። ድሬዳዋ ከተማ በ35 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ43 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ባለፉት ሰባት የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው ድሬዳዋ ከተማ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት በሚያደርገው ትግል ሶስት ነጥብ ያስፈልገዋል። በ33ኛ ሳምንት ሃዋሳ ከተማን 1 ለ 0 ያሸነፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ በድል ጉዞው ለመቀጠል ይጫወታል። ሃዋሳ ከተማ ከኢትዮጵያ ቡና ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ባለፉት 10 የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው ሃዋሳ ከተማ በ45 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ ቡና በ46 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ33ኛ ሳምንት ፋሲል ከነማን 2 ለ 1 በማሸነፍ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ኢትዮጵያ ቡና ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ወደ ሜዳ ይገባል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር እስከ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ሲዳማ ቡና በ58 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና በ14 ጎሎች እየመራ ይገኛል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኮቹ ናትናኤል ዳንኤል እና አዲስ ግደይ፣ የፋሲል ከነማው ታምራት ኢያሱ በተመሳሳይ 11 ግቦች ይከተላሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በሐረሪ ክልል ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል
May 28, 2026 170
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን የክልሉ የግብርና ልማት ቢሮ አስታውቋል። የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ነስረዲን አህመድ እንደገለጹት በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ይተከላሉ። ከሚተከሉ ችግኞች ውስጥም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የፍራፍሬና የደን ችግኞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም ከ200 ሺህ በላይ የሚሆኑት ለእንስሳት መኖ የሚያገለግሉ ችግኞች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የችግኝ ጣቢያዎች እየተከናወነ በሚገኘው ስራም ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን አንስተዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር እስከ አሁን የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት የክልሉን የደን ሽፋን በማሳደግና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሻሻሉ መምጣታቸውንም ነው የተናገሩት።
የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውን ችግኞች ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ ነው
May 28, 2026 213
ሚዛን አማን፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውን የቡና፣ የቅመማቅመም እና የፍራፍሬ ችግኞች ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑን ገለጸ። ማዕከሉ በገበያ ተፈላጊ የሆኑ የካካዎ፣ የቫኔላና ሌሎች የቅመማቅመም ችግኞችን ለመጪው ክረምት ተከላ ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑን አስታውቋል። የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ደረጀ ቱሉ (ደ/ር) እንዳሉት፣ ማዕከሉ የአርሶ አደሩን ምርታማነት የሚያሻሽሉና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ከ70ዐ ሺህ በላይ የቅመማቅመም ችግኞችን እያዘጋጀ ይገኛል። ችግኞቹ በመጪው ክረምት የሚተከሉ ሲሆን ለአካባቢ ሥነ ምህዳር ተስማሚና ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በክረምቱ የሚተከሉ ችግኞች ምርታማነታቸው ከፍ ያለ ከመሆኑ በላይ የአካባቢው ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ ተደማሪ አቅም እንደሚሆኑም አስረድተዋል። የሸካ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አለምሰገድ ኃይለኢየሱስ በበኩላቸው ማዕከሉ ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ የቅመማቅመምና ሌሎች ችግኞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረቡን ተናግረዋል። በዚህም የአርሶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ እንደቻለ አክለዋል። ተግባሩን በማስቀጠልም ማዕከሉ በበጋ ወራት ያፈላቸውን ችግኞች ለክረምቱ ወቅት ተከላ ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑንም ገልጸዋል። በዞኑ የየኪ ወረዳ አርሶ አደር መሐመድ ታዬ እና አርሶ አደር አየለች አናሞ በበኩላቸው ከምርምር ማዕከሉ የሚቀርቡ ዝርያዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጡና ምርታማነታቸው ያደገ መሆኑን በተግባር ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል። ዘንድሮ በራሳቸው ያዘጋጁትንና በማዕከሉ የተዘጋጁ ችግኞችን በመትከል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ወደ ሥራ መግባታችውን አመልክተዋል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል
May 25, 2026 1071
አዳማ፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መደረጉን የምሥራቅ ሸዋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በይፋ ከተጀመረ ጀምሮ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል። ይህም የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተጨባጭ በማረጋገጥ ውጤት ማስገኘቱን ጠቁመው፤ የሰብል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የጎላ አስተዋጽዖ ማበርከቱን ለአብነት ጠቅሰዋል። ለዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብርም ለደን ልማት የሚሆኑ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው 269 ነጥብ 5 ሚሊየን ችግኞች በሁሉም ወረዳዎች ችግኝ ጣቢያዎች አማካኝነት መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። ዘንድሮ በ45 ሺህ 563 ሔክታር ላይ የችግኝ ተከላ እንደሚካሄድም ነው ያመላከቱት።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለቀጣናው ብልፅግና የላቀ ሚና አለው
May 23, 2026 1144
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር እንዲሁም ብልፅግናን ለማጎልበት የላቀ ሚና እንዳለው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የራሷን የተፈጥሮ ሀብት ከመንከባከብ ባለፈ፣ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚከሰቱ አደጋዎችን በጋራ ለመከላከል የአካባቢውን አገራት አብሮ የመልማት ዕቅድ ይዛ እየሠራች ስለመሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህም በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለጎረቤት አገራት በርካታ ችግኞችን ማበርከቷ ይታወቃል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚከሰቱ የተፈጥሮ መዛባቶችን ለመከላከል፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና አካባቢን ለመታደግ ታስቦ በከፍተኛ ሀገራዊ ቁርጠኝነት እየተተገበረ የሚገኝ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው። ይህ ንቅናቄ በአገር ውስጥ ካስገኛቸው ሁለንተናዊ ጥቅሞች ባሻገር፣ ለጎረቤት አገራትና ለጠቅላላው የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ የምታከናውነው የተፈጥሮ ጥበቃ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለቀጣናው አገሮች የሚተርፍ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ነው፡፡ የኢጋድ ሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በቀጣናው እንደ ጎርፍ፣ የበረሃ አንበጣ እና ድርቅ ያሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎች የሰዎችን መፈናቀልና ስደት ይፈጥራሉ፡፡ በዚህም ዜጎች ከአካባቢያቸው ችግሩ ወደ ሌለባቸው አካባቢዎችና ድንበሮችን አቋርጠው የሚሰደዱበትን ሁኔታ የሚፈጠር ሲሆን፤ ይህም በቀጣናው ላይ የሚያሳድረው ጫና ቀላል እንዳልሆነ አመልክተዋል። ይህንን ተግዳሮት ለመቋቋም በኢትዮጵያ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ውጤቶችን እያሳየ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ አሁን ላይ የሚታየው መደበኛ የዝናብ ሁኔታ ስኬት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ተከትሎ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እየተጠናከረ በሄደ ቁጥር በቀጣናው የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር፣ ሰላምና ብልፅግናን ለማጎልበት የራሱ የሆነ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው አንስተዋል። ይህንን የኢትዮጵያን መልካም ተሞክሮ በመረዳት እንደ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ጅቡቲ ያሉ የጎረቤት አገራት ተመሳሳይ አረንጓዴ ልማቶችን እየተከተሉ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ከዋና ዋና ዓላማዎቹ መካከል አንዱ የግብርና እና የአካባቢ ጥበቃ ልማት መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ ይህንን የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ሀሳብ በጽኑ እንደሚደግፈው ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ባለፉት ዓመታት በከፍተኛ ተነሳሽነት ሲተገበር ቆይቷል። በመርሀግብሩ እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ጉልህ ድርሻ እየተጫወተ ይገኛል። ይህ ግዙፍ ብሔራዊ የልማት ፕሮጀክት በኅብረተሰቡ ዘንድ ችግኞችን የመትከልና የመንከባከብ በጎ ባህል እንዲዳብርና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ እንዲያድግ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል። በተለይም በችግኝ ማፍላት፣ በተከላና ተያያዥ ሥራዎች ላይ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር በሀገሪቱ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ላይ አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 1140
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 3177
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 2021
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 1936
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 1339
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው። መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል። በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል። ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል። በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል። በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ። በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 2299
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 2538
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 2350
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 2276
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 1057
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት
May 17, 2026 4595
በኢዜአ ዐይን …! በዮሐንስ ደርበው እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉን የሚሉ እሮሮዎች በተለያዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሲነሱ ቆይተዋል። በተለይም በአንዳንድ ተቋማት መንግሥታዊ አገልግሎት ለማግኘት እዚያም እዚህም መንከራተት፤ደግሞም ወረፋ በመጠበቅ መጉላላት ብሎም ለጊዜና ገንዘብ ወጪ መዳረግ ይስተዋላል የሚሉ ሐሳቦች ተስተጋብተዋል። ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ባሳለፍነው ሳምንት … መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል አሠራር በመንደፍ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ አስጀመረ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማዕከሉ አገልግሎት ባስጀመሩበት ወቅትም ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው ብለው ነበር። አሁን ላይም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ነው።መስፋፋቱም በማዕከላት ብዛት፣በአገልግሎት መስጫ መስኮቶች ቁጥር እና በአገልግሎት ዐይነቶች እየተገለጠ ነው። በዚህም በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት የተደራጁ ሲሆን ይህ አሃዝም ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እና ያለውን ፈጣን እድገት ያመላክታል። ጉዳዩ የዜጎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ማላቅ፤ ብልሹ አሠራርንም መቅረፍ ነውና መንግሥት በልዩ ትኩረት ይዞታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ አሥተዳደርና በሐረሪ ክልል ጉብኝት ባደረጉበት ወቅትም፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የምልከታቸው አካል ማድረጋቸው ለጉዳዩ የተሰጠውን ከፍያለ ትኩረት ያሳያል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሶብ የሞባይል አገልግሎትን በመረቁበት ወቅት ደግሞ፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ብለዋል። አክለውም፤በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች ዕርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል፤ ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፤ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ መሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል ማለቱም ይታወቃል። የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ደግሞ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ ያስቻለ ስኬት ተገኝቷል ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ የመንግሥት አገልግሎቶችም ዜጋ ተኮር፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አብራርተዋል። በዲጂታል 2030 የአገልግሎት አሰጣጥ አመላካች ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚጠቀሱ 50 ሀገራት መካከል አንዷ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ዜጎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በኦንላይን በየትኛውም ቦታ ሁሉንም አገልግሎቶች እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ ስለመሆኑም እንዲሁ። አገልገሎቱን ያገኙ አስተያየት ሰጭዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ እንግልትን ያስቀረ፣ ጊዜና ወጭን የቀነሰ ነውና ይስፋፋ፤ ተጠናክሮም ይቀጥል። #መሶብ_የአንድ_ማዕከል_አገልግሎት #የዜጎችን_እንግልትና_ብልሹአሠራርን_መቅረፍ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #በኢዜአ_ዐይን
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 17, 2026 2642
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 2 እስከ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ጋር መምከራቸው ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም በኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል። ለነበረን ጠቃሚ የሐሳብ ልውውጥና ቀጣይነት ላለው አጋርነትም ምስጋናዬ የላቀ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ በኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና በፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በጋራ አዘጋጅነት በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካፍለዋል። በዚሁ ወቅትም በተለይም የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት እና የኃይል ሽግግርን በተመለከተው ውይይት ላይ ከተሞክሯችን የተቀዱ ከፍ ያሉ ሐሳቦች ተነስተዋል ብለዋል። አክለውም፤ ኢትዮጵያ በተነሱት ሁለት ዘርፎች የጀመረችውን ሥራ በማጠናከር የላቀ ሚና መጫወቷን ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንኳን ደህና መጡ ስል ሁልጊዜም በልዩ ኩራትና ደስታ ነው ሲሉ ተቀብለዋቸዋል። ከአቀባበሉ በኋላም፤ መሪዎች በጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በዚህም መሠረት፤ በታዳሽ፣ የተቀናጀ እና ዘላቂ ኃይል እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራምን ለመተግበር የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ ብድርን ጨምሮ የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የመንግሥትና የግል አጋርነት አዲስ የማዕቀፍ እና የፍኖተ ካርታ ስምምነት ተፈርሟል። · ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ማውጣቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርገዋል። እነዚህ አራት ቴምብሮች እ.ኤ.አ. በ1945 በሳን ፍራንሲስኮ የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን ከመፈረም ጀምሮ፤ በኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን እስከማሰማራት እና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ እስከ ማስተናገድ ያለውን የጋራ ታሪካችንን የሚተርኩ ናቸው ብለዋል። በዓለም የፖስታ ኅብረት በኩል ለ192 ሀገራት የተሰራጩት እነዚህ ቴምብሮች፤ ለአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን ለትውልድ ሁሉ የሚተርፍ የታሪክ ዐሻራ ማሳያ መሆናቸውንም አስታውቀዋል። በተያያያዘም፤ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ በዘመናዊው ታሪክ ውስጥ እጅግ ፈታኝ በሆነ ወቅት ላይ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር ጥልቅ አድናቆታችንን እንገልጻለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የተባበሩት መንግሥታት የጸናው ሀገራት ከመከፋፈል ይልቅ ውይይትን ስለመረጡ መሆኑን አስገንዝበው፤ ኢትዮጵያም ይህንኑ የሁልጊዜ ምርጫዋን ታጸናለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም የምክክር ባህል እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበው፤ ጠንካራ የሲቪክ ማኅበረሰብ ባህል ግንባታ ደግሞ ያላሰለሰ የመነጋገር ልምምድ እና የሰከነ የወል መደማመጥን ግድ ይላል ብለዋል። የእስካሁን ሂደቱም በማኅበረሰባችን በየደረጃው የመደማመጥን ከፍ ያለ ጠቀሜታ አሳይቷል ሲሉም ገልጸዋል። ሂደቱ በሀገራችን ሁሉም ማዕዘናት የሚገኙ ከ90 በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን አመለካከቶች እና የውይይት ውጤቶች ያንፀባረቀ ሆኗልም ነው ያሉት። ለሀገር ወሳኝ ፋይዳ የያዘው የምክክሩ ምዕራፍ ተጨባጭ ውጤት ወደሚያስገኘው ቀጣይ ምዕራፍ በሚሸጋገርበት በዚህ ወቅት፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለሀገራችን ሰላም፣ አንድነት እና ዘላቂ መረጋጋትን የሚያረጋግጥ የጋራ ፅኑ አቋም እና ገንቢ በሆነ መንገድ አስተዋፅኦ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል። · የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን በመረቁበት ወቅት፤ ፓርኩ አስተማማኝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጀመርነው የብልጽግና ጉዞ ተደማሪ እመርታ ነው ብለዋል። ለመካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች ምቹ የንግድ ከባቢ ከመፍጠር ባሻገር በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶቻችን የሥራ ዕድል ይከፍታል ሲሉም ገልፀዋል። ፓርኩ የሀገራችን አምራቾች አቅማቸውን በማጎልበት፣ ምርታማነታቸውን ማሳደግና ተወዳዳሪነታቸውን በመጨመር ለከተማችን፣ ለሀገራችንና ለቀጣናው የሚተርፉበት ታላቅ እድልን ይዟል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተኪ ምርቶችን በማምረት በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛና ቀልጣፋ የንግድ ትስስር ይፈጥራል፤ ምርቶችን ደግሞ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይጫወታል ሲሉ አስረድተዋል። · ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ መጀመር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔን ባስጀመሩበት ወቅት፤ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ቆራጥ ጥረት ውስጥ የሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል በማድረግ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በመላ ሀገሪቱ ከ35 ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት የነጻና አስገዳጅ ትምህርት ተደራሽ እንዲሆን እያደረግን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር ላይ መሥራት በመሆኑ ተባብረን፣ በጊዜ የለንም መንፈስና በትጋት እንሥራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። · የፖሊሲ ቀን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ ባሳላፍነው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው የፖሊሲ ቀን ተከብሯል። በዚሁ ወቅትም፤ ውጤታማ ፖሊሲ ለሀገራዊ ዕድገት የጀርባ አጥንት መሆኑን አስገንዝበው፤ መንግሥት በግልፅ፣ ተተግባሪና ጥራት ባላቸው ፖሊሲዎቹ ለሕዝብ የገባውን ቃል እየተገበረ ስኬትም እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ሀገራችን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ በጂኦ-ፖለቲካዊና በቴክኖሎጂ ለውጦች ላይ ቀድሞ ምላሽ የሚሰጡ ጥናቶች ያስፈልጋሉ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በዕውቀት ላይ ኢንቨስት በማድረግ እና ለማስረጃዎች ዋጋ በመስጠት፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ የፖሊሲ ሥነ-ምኅዳር ለመገንባት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ለዚህ ስኬት ሁላችንም በጋራ እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 8386
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 4954
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 10732
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 9213
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 3006
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 3008
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።