ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ቦርዱ የምርጫ ውጤቶችን ይፋ የሚያደርግበትን የድህረ-ምርጫ ተግባራት ለጋዜጠኞች አስጎበኘ  
Jun 11, 2026 410
አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ውጤቶችን ይፋ የሚያደርግበትን የድህረ-ምርጫ ተግባራት ለጋዜጠኞች አስጎበኘ። የምርጫ ቦርድ ውጤት ማረጋገጫ ክፍል አስተባባሪ ዶክተር ሽመልስ ሲሳይ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በሁሉም ምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ የተጠናቀቀላቸው ሙሉ ሰነዶች በቀጥታ ወደ ዋናው የቦርዱ ውጤት መረከቢያ ክፍል ይገባሉ። በመቀጠልም በማረጋገጫ ክፍሉ ውስጥ እያንዳንዱ ዕጩ ያገኘው ድምፅ ዋጋ ካላቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች፣ እንዲሁም በዕለቱ በአካል ተገኝተው ከፈረሙ መራጮች ቁጥር ጋር የመጣጣሙ ጉዳይ በጥብቅ እንደሚፈተሽ ተናግረዋል።   አስተባባሪው ዶክተር ሽመልስ እንደገለጹት፤ ይህን የማጣራት ሂደት የሚያልፉ መረጃዎች ተገቢነትና ትክክለኛነታቸውን ወደ ሚያረጋግጠው የኦዲት ቡድን የሚመሩ ይሆናል። ትክክለኛነታቸው የተረጋገጠው ደግሞ በቦርዱ የአይሲቲ (ICT) ሲስተም ውስጥ ገብተው በቦርዱ እንዲጸድቁ ይደረጋልም ነው ያሉት። በማረጋገጥ ሂደቱ ላይ ያልተጣጣሙና ግድፈት ያለባቸው መረጃዎች ሲገኙ የኦዲት ቡድኑ በሚገባ ከመረመረ በኋላ ለውሳኔ የሚያቀርብ ሲሆን፤ ቦርዱም እነዚህን ጥብቅ የአሠራር ሂደቶች በሙሉ ተከትሎ የመጨረሻውን ውጤት ይፋ ያደርጋል ብለዋል።
ዋና ጠቅላይ መምሪያው ከተሰጠው ተልዕኮ በተጨማሪ የሀገርን ክብር በአደባባይ ከፍ የሚያደርጉ ስፖርተኞችን እያፈራ ይገኛል
Jun 11, 2026 263
አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከተጣለበት ሰላምን የማስጠበቅ ተልዕኮ በተጨማሪ የሀገርን ክብር በዓለም መድረክ ከፍ የሚያደርጉ ስፖርተኞችን እያፈራ እንደሚገኝ የመምሪያው አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ ገለጹ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በ2018 ዓ.ም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የፖሊስ አባል ስፖርተኞች የማዕረግ እድገት፣ የገንዘብ ሽልማት እንዲሁም የእውቅናና ምስጋና መርሃ-ግብር አካሂዷል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ፍጹም ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፖሊስ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ለዚህም ለመዲናዋ የፖሊስ አባላት በሙሉ የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከተጣለበት ሰላምን የማስጠበቅ ተልዕኮ በተጨማሪ የሀገርን ክብር በዓለም አቀፍ የስፖርት አደባባይ ከፍ የሚያደርጉ ስፖርተኞችን እያፈራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከተቋሙ የሚወጡ ስፖርተኞች በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ውድድሮች ድልን በመቀዳጀት በርካታ ሜዳሊያዎችን በማስመዝገብ የሀገሪቷ ክብር በዓለም አደባባይ ጎልቶ እንዲታይ አድርገዋል ብለዋል። ይህ አበረታች ውጤት ሊገኝ የቻለው ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ እንደሆነም ተናግረዋል። የተካሄደው የእውቅና መርሃ ግብር ባለድል ስፖርተኞችን ለማበረታታት ያለመ ሲሆን፤ በቀጣይም የፖሊስ ተቋማት የተተኪ ስፖርተኞች ምንጭ ሆነው እንዲቀጥሉ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው
Jun 11, 2026 313
ወላይታ ሶዶ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የደቡብ ማዕከል አስታወቀ። ማዕከሉ በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በግብርና ልማት ሥራ የተሰማሩ ኩባንያዎች ተግባራት አፈጻጸምን የሚገመግም መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል።   በኢንስቲትዩቱ የደቡብ ማዕከል የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ዳይሬክተር አቶ ተሰማ ህርባዬ እንዳሉት፤ አርሶ አደሮችን በኩታ ገጠም ግብርና ቢዝነስ ኩባንያዎች በማደራጀት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየተሰራ ነው። ለዚህም ማዕከሉ በተመረጡ ወረዳዎች በኩታ ገጠም እርሻ አርሶ አደሮችን በማደራጀት ምርታማነታቸው እንዲያድግና የገበያ ትስስር እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ኩታ ገጠም እርሻ አርሶ አደሩ የግብአት አቅርቦትን በቀላሉ የሚያገኝበት አውድ ከመፍጠሩ ባለፈ የሜካናይዝድ እርሻን በመተግበር ምርትና ምርታማነቱን ለማሳደግ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል። ኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አድማሱ አወቀ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በክልሉ ግብርናን በማዘመን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ ነው።   ለዚህም ቢሮው ከግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሮች እያደረሰ ይገኛል ብለዋል። ይህም አርሶ አደሩ የግብርና ምርቶቹን በጥራትና በብዛት ለገበያ በማቅረብ ተወዳዳሪ እንደሚያደርገው ነው የተናገሩት። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን የቸሃ ወረዳ ግብርና ቢዝነስ ኩባንያ አባል አርሶ አደር አብዱራሃማን ሙክታር፤ ከዚህ ቀደም በተናጠል ባከናወኑት የእርሻ ስራ ብዙም ሳይጠቀሙ ቆይተዋል።   በአሁኑ ወቅት በኩታ ገጠም እርሻ ተደራጅተው ኩባንያ ከፈጠሩ ወዲህ ጉልበታቸውን በማስተባበር እንዲሁም ግብአትና ቴክኖሎጂ በመጠቀም ምርታማነታቸውን እንዳሳደጉ ተናግረዋል። ይህም ምርታቸውን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ የተሻለ ገቢ በማግኘት የቤተሰባቸውን ኑሮ ለማሻሻል እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። በስልጤ ዞን የሳንኩራ ወረዳ ግብርና ቢዝነስ ኩባንያ አባል ወይዘሮ አሚና ሃጂ ጀማል በበኩላቸው፤ 85 ወንዶች እና 15 ሴቶች በግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ተደራጅተው የጓሮ አትክልትና ሌሎች ምርቶች እያመረቱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።   በዚህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚ እየሆኑ ከመምጣታቸው ባለፈ ገበያን በማረጋጋት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከማዕከላዊ እና ከሲዳማ ክልሎች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በክልሉ ተማሪዎች በክልል አቀፍ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆኑ የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል
Jun 11, 2026 336
ወራቤ ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በክልል የተማሪዎችን ብቃትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ በክልል አቀፍ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆኑ መሰራቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ ክልላዊ የፈተና ዝግጅትን በማስመልከት ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በክልሉ አዲሱን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ የተማሪዎችን ብቃትና ተወዳዳሪነት ማሳደግ ተችሏል። የተማሪዎችን ብቃትና ተወዳዳሪነት ለመለካት ዘንድሮ በሚሰጠው የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናም ከ183 ሺህ 790 በላይ ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ተናግረዋል። በክልል ደረጃ የሚሰጠውን ፈተና ውጤታማ ለማድረግ ተማሪዎች በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ሲሰራ መቆየቱንም ነው አቶ አንተነህ የገለጹት። ለዚህም ከመደበኛ የመማር ማስተማር ሥራው በተጨማሪ በማጠናከሪያ ትምህርት ተማሪዎችን የማብቃት ሥራ ተከናውኗል ብለዋል። ተማሪዎች ኩረጃን በመጸየፍ የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲያመጡ በስነልቦና የተሰራው ስራም ውጤት እያስገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን በተገቢው ለመምራትም 139 በላይ ፈታኝ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮችና ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የመፈተኛ ማዕከላት መዘጋጀታቸውን ነውያስታወቁት። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አያይዘውም 3ኛው ዙር ክልል አቀፍ የሳይንስና ፈጠራ ሥራዎች አውደ ርዕይና ኤግዚቢሽን ነገ በቡታጅራ ከተማ እንደሚካሄድ አመልክተዋል። በኤግዚቢሽኑ በተማሪዎች፣ በመምህራን፣ በግል ፈጠራ ባለቤቶች እና በፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የተሰሩ የፈጠራ ሥራዎች ለውድድር እንደሚቀርቡም ገልጸዋል። የማህበረሰቡን ችግር ለሚፈቱ የፈጠራ ሥራዎች የገበያ ትስስር ከማመቻቸት ባለፈ ማበረታቻና እውቅና እንደሚሰጥም ተናግረዋል። በክልሉ የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ታውቋል።  
የሚታይ
የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በሁሉም የኢኮኖሚ አመላካቾች የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ታሳቢ ያደረገ ነው
Jun 11, 2026 418
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በሁሉም የኢኮኖሚ አመላካቾች የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ፡፡ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 25ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት የበጀት መግለጫ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡   ምክር ቤቱም በቀረበው የ2019 የበጀት መግለጫ ላይ ከተወያየ በኋላ ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ መርቶታል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ለምክር ቤት ባቀረቡት የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ እንደገለጹት፤ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውና የአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ ትግበራ ስኬታማ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጣዊና ውጫዊ ጫናዎችን በብቃት በመቋቋም ጠንካራ አፈጻጸም ማስመዝገቡን ገልጸው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው አበርክቶ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከ2012 እስከ 2016 ባሉት የበጀት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአማካይ በየዓመቱ የ6 ነጥብ 8 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ እንደነበር በማስታወስ፤ በ2017 በጀት ዓመት የ9 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት የመካከለኛው ምሥራቅ የተፈጠረውን ዓለም አቀፍ ጫና ጭምር በመቋቋም የ10 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ታስመዘግባለች ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ በዓለም ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት ተርታ የሚያሰልፋትን ስኬት ማስመዝገቧን ገልጸው፤ ይህም የተቀናጀ የገንዘብና ፊሲካል ፖሊሲው ውጤት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡   ይሄውም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በጠንካራ መሠረት ላይ የተገነባ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ የሸቀጦችን የዋጋ ግሽበት ወደ ነጠላ አሃዝ ማውረድ አስችሏል ብለዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት የኢኮኖሚ አፈጻጸሙ በጥሩ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኝ በማንሳት፤ ስኬቱ የተረጋጋና የበለጸገ ኢኮኖሚ ለመገንባት የተጀመረውን ጥረት እንደሚያጠናክር ገልጸዋል፡፡ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትም በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በሁሉም የኢኮኖሚ አመላካቾች የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡ በ2019 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 10 ነጥብ 1 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብ እንደሚጠበቅና የቀረበው ረቂቅ በጀትም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተሳካ ሁኔታ ገቢራዊ ለማድረግና የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የሚፈጥረውን የኢኮኖሚ ጫና ጨምሮ የውጭ ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን ለመቋቋም ያለመ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የፌደራል መንግስትን ጠቅላላ ገቢ 1 ነጥብ 817 ትሪሊየን ብር ለማድረስ ታሳቢ መደረጉን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 6 ትሪሊየን ብር የሚሆነው ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱን አመላክተዋል። ለ2019 በጀት ዓመት የቀረበው አጠቃላይ 2 ነጥብ 339 ትሪሊየን ብር በጀት ከዘንድሮው በጀት ዓመት አንጻር የ21 ነጥብ 3 በመቶ እድገት እንዳለው ገልጸዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በተለያዩ ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቧን ገልጸዋል፡፡ ሪፎርሙ የውጭ ምንዛሪ በገበያ እንዲወሰን በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ክምችትን ማሳደግ፣ የዋጋ ግሽበትን ወደ ነጠላ አሃዝ መውረድና የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰትን ማሳደግ አስችሏል ብለዋል፡፡ ለ2019 በጀት ዓመት የቀረበው ረቂቅ በጀት ከባለፈው ዓመት የላቀ መሆኑ የመንግሥትን ግዙፍ የልማት ዕቅዶች ለማሳካት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ ስኬታማ ውጤቶች ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ማዕከል አድርጓታል
Jun 11, 2026 376
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ ስኬታማ ውጤቶች ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ማዕከል ተደርጋ እንድትታይ ማድረጉን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ገለጹ። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 25ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።   በስብሰባውም የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የፌዴራል መንግሥት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን በተመለከተ በሚያቀርቡት የበጀት መግለጫ ላይ ይወያያል። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ፤ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የቀረበውን የፌዴራል መንግሥት የ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ መግለጫ አቅርበዋል። በመግለጫቸው፤ ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ በተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ክፍያ ሚዛን ጫናና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ተግዳሮቶችን በእጅጉ መቅረፍ ተችሏል ብለዋል። የገበያ መር የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ሽግግሩም የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ከመቅረፉ ባለፈ፣ በሕጋዊና በትይዩ (ጥቁር) ገበያ መካከል የነበረውን የተመን ክፍተት በከፍተኛ ደረጃ አጥብቦታል ብለዋል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት የሸቀጦች ወጪ ንግድ ገቢ በ2016 ከነበረበት 3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር ወደ 8 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ዕድገት በማስመዝገብ የ119 በመቶ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል። በመገባደድ ላይ በሚገኘው በዚህ በጀት ዓመትም የወጪ ንግድ ከፍተኛ አፈጻጸም በመቀጠሉ የንግድ ሚዛን ጉድለቱ በከፍተኛ ደረጃ ቀንሷል ብለዋል። ከዚህ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ኃይል ማመንጨቱ ምርታማነትን ከመጨመር ባለፈ፣ ጎረቤት ሀገራትን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ በማድረግ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል። የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያውን በተመለከተም፤ ማሻሻያው የፋይናንስ ዘርፉን ውጤታማና ጤናማነት በማረጋገጥ የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያሳልጥ ዘመናዊና ገበያ መር የወለድ ምጣኔ እንዲፈጠር ማድረጉን አስረድተዋል። ይህም የንግድ ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር በገበያ ሁኔታዎች ላይ በመመስረት የወለድ ተመኖችን እንዲደራደሩና እንዲወስኑ ሙሉ መብት አስገኝቶላቸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም የተዘረጋውን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ የሚያጠናክሩ በርካታ ለውጦችን በመተግበር የፋይናንስ ዘርፉን ደህንነት ለማስጠበቅና ለማዘመን እየሠራ ይገኛል። እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰነደ መዋለ ንዋይ (ካፒታል) ገበያ መመስረቱ ዘመናዊ የካፒታል ሥርዓትን በመዘርጋት፣መንግሥትና ኩባንያዎች የረጅም ጊዜ የፋይናንስ ፍላጎታቸውን ማሰባሰብ የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዝቅተኛ ገቢ ባለው የሕብረተሰብ ክፍል ላይ የሚያስከትለውን የኑሮ ጫና ለመቋቋም መንግሥት ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ የማኅበራዊ ድጎማ ወጪዎችን ተግባራዊ ማድረጉን ሚኒስትሩ አብራርተዋል። በዚህም መሠረት በነዳጅ፣ በአፈር ማዳበሪያ፣ በልማታዊ ሴፍቲኔት፣ በምግብ ዘይት፣ በመሠረታዊ መድኃኒቶች እንዲሁም በፌዴራልና በክልል የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ላይ ከፍተኛ የበጀት ድጎማ ተደርጓል። ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡት የኢኮኖሚ ዕድገት ውጤቶች የውጭ ባለሀብቶችን ቀልብ በመሳብ ኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት መዳረሻቸው እያደረጓት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአጠቃላይ በተያዘው በጀት ዓመት የ10 ነጥብ 2 በመቶ ጥቅል ሀገራዊ ዕድገት (GDP) ማስመዝገብ እንደሚቻል በርካታ የኢኮኖሚ አመላካቾች ያሳያሉ ብለዋል።
በአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን ከኢኮኖሚ ፍላጎት ጋር የሚያጣጥም ክህሎትና ብቃት ልማት ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይገባል
Jun 11, 2026 336
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን ከኢኮኖሚ ፍላጎት ጋር የሚያጣጥም የዜጎች ክህሎትና ብቃት ልማት ላይ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚገባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክሌቨር ጋቴቴ ገለጹ። በሥራ ፈጠራ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የአፍሪካ ዴቨሎፕመንት ኢምፓክት ፎረም 2026 በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) መካሄድ ጀምሯል። የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክሌቨር ጋቴቴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የአፍሪካን መጻኢ ዕድል ለመወሰን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ኢንዱስትሪ ምኅዳር መገንባት ይገባል ብለዋል። ከዓለም አቀፍ አኳያም አህጉሪቷ የታደለችውን ስትራቴጂክ የሰው ሃብት የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት በማረጋገጥ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም የአፍሪካ ሀገራት መንግሥታት፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሥራ ፈጣሪዎች፣ የልማት ተቋማትና የግል ማኅበራት አዳዲስ መፍትሄዎችን እያፈለቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ፎረሙም የአፍሪካዊያንን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማሻሻል ተግባራዊ መፍትሄዎችን ለማራመድ ፖሊሲ አውጪዎችን፣ ባለሀብቶችንና የልማት አጋሮችን የሚያገናኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የአህጉሪቷ ዜጎችን በሚፈለገው መጠን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ ሁሉንም ያካተተ ምቹ ሥነ-ምህዳር መገንባት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። ለዚህም ከአፍሪካ የኢኮኖሚ ዕድገት ፋላጎቶች ጋር የሚጣጣሙ የዜጎች ክህሎትና ብቃት የሚያጎለብት ኢንቨስትመንትን ማሳደግ እንዲገባ አስገንዝበዋል። ለወጣቶችም የትምህርት ሥርዓቶችን የሚያጠናክር የዲጂታል ስልጠና በማሳደግ በነባርም ሆነ አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ክህሎቶች ማስታጠቅ እንደሚገባ ተናግረዋል። ለዚህም አዳዲስ ጀማሪ ስራዎችን (start-ups) መደገፍ እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካን ኢንዱስትሪ ልማት ከእሴት ሰንሰለት ጋር በማሰናሰል የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልጽግናን ማፋጠን እንደሚያስፈል ጠቁመዋል። አፍሪካ ጥሬ ዕቃዎችን ወደ ውጭ በመላክ እና የተጠናቀቁ ምርቶችን ወደ ውስጥ በማስገባት በቂ የሥራ ዕድል መፍጠር እንደማትችል አጽንኦት ሰጥተዋል።
ጽንፈኛ ቡድኑ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይሳካ ያደረገው ሙከራ በሰላም ወዳዱ ሕዝብ ህልም ሆኖ ቀርቷል-አቶ ጣሂር መሀመድ
Jun 11, 2026 719
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ ጽንፈኛ ቡድኑ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይሳካ ያደረገው ሙከራ በሰላም ወዳዱ ሕዝብ ህልም ሆኖ መቅረቱን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አባል አቶ ጣሂር መሀመድ ገለጹ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ተሳትፎ ጎልቶ የታየበት ስኬታማ ሆኖ ተጠናቋል። ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ታዛቢዎች ምርጫው ዲሞክራሲያዊ፣ አካታችና ምሳሌነቱ የሚጠቀስ መሆኑን እማኝነታቸውን ሰጥተዋል። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አባል አቶ ጣሂር መሀመድ በምርጫውና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። አቶ ጣሂር እንዳሉት፤ የአማራ ክልል ሕዝብ በነጻነት የራሱን መሪዎች እንዳይመርጥ ጽንፈኛው ቡድን ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ጭምር በመቀናጀት ምርጫውን የማደናቀፍ ተግባራት ላይ ተጠምዶ መቆየቱን አንስተዋል። ጽንፈኛው ቡድን መራጩን ሕዝብ በዚህ ምርጫ ትሳተፍና፣ ይሄን ታደርግና የሚሉ ዛቻና ማስፈራሪያዎች ጭምር በመጠቀም አደገኛ ቅስቀሳዎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ በመሰል እንቅስቃሴዎች ሕዝቡ ዋጋ ሲከፍል መቆየቱን ጠቅሰዋል። እንዲያም ሆኖ የአማራ ክልል ሕዝብ ጫናዎችን ተቋቁሞ ለሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ በመስጠት ምርጫውን እንዲሳካ አድርጓል ያሉት አቶ ጣሂር፤ ለዚህ በሳል ውሳኔ ሕዝቡ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል። በዚህ ሁሉ ጫና ውስጥ ሕዝቡ ወጥቼ እመርጣለሁ፤ የምፈልገው መደበኛ የሆነ የመንግሥት አስተዳደር ነው በሚል መርህ በመመራት ምርጫውን ማሳካቱ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም በተጻጻሪው የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን የአማራን ሕዝብ እንደማይገልጸው ማሳያ መሆኑንም አስረድተዋል። በሕዝቡ ድምጽ የሚመሰረተው መንግሥት ዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሰራ እንደሚገባ ያመላከተ ነው ያሉት አቶ ጣሂር፤ ሕዝቡ በሰላም ዙሪያ በሚሰሩ ሥራዎች ተባባሪና ቁርጠኛ መሆኑን ያሳየበት ምርጫ መሆኑንም አብራርተዋል። በአማራ ክልል የተካሄደው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የክልሉ የጸጥታ ኃይልና ሚሊሻዎች በየደረጃው ካሉ አመራር ጋር በቅንጅት ያከናወኑት ተግባር ጉልህ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል። ይሄ ውጤት ደግሞ በመንግሥት እና በመደበኛ ሥርዓት ሕዝቡ እንዲተማመን ያስቻለ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ጣሂር ገለጻ፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚጋፋ የኃይል አሰላለፍ ሕዝብንም ሀገርንም ዋጋ የሚያስከፍል በመሆኑ ሕዝቡ በዚህ ላይ ግንዛቤ ጨብጦ ለሰላምና ዴሞክራሲ ግንባታ የራሱን አሻራ እንዲያሳርፍ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ እየሰራ ነው። "ጥያቄዎች የሚመለሱት በኃይል ነው" የሚል አቋም ይዘው እየተንቀሳቀሱ ያሉ አካላት ሰላማዊ መንገድን በመምረጥ ችግሮች በውይይት የሚፈቱበት አውድ መፍጠር ላይ ሊሰሩ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። መንግሥት የሰላም ጥሪ አቅርቦ በሩን ክፍት ማድረጉ የሚበረታታ መሆኑን አመልክተው፤ ይሄ ሥራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመልክተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ቦርዱ የምርጫ ውጤቶችን ይፋ የሚያደርግበትን የድህረ-ምርጫ ተግባራት ለጋዜጠኞች አስጎበኘ  
Jun 11, 2026 410
አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ውጤቶችን ይፋ የሚያደርግበትን የድህረ-ምርጫ ተግባራት ለጋዜጠኞች አስጎበኘ። የምርጫ ቦርድ ውጤት ማረጋገጫ ክፍል አስተባባሪ ዶክተር ሽመልስ ሲሳይ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በሁሉም ምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ የተጠናቀቀላቸው ሙሉ ሰነዶች በቀጥታ ወደ ዋናው የቦርዱ ውጤት መረከቢያ ክፍል ይገባሉ። በመቀጠልም በማረጋገጫ ክፍሉ ውስጥ እያንዳንዱ ዕጩ ያገኘው ድምፅ ዋጋ ካላቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች፣ እንዲሁም በዕለቱ በአካል ተገኝተው ከፈረሙ መራጮች ቁጥር ጋር የመጣጣሙ ጉዳይ በጥብቅ እንደሚፈተሽ ተናግረዋል።   አስተባባሪው ዶክተር ሽመልስ እንደገለጹት፤ ይህን የማጣራት ሂደት የሚያልፉ መረጃዎች ተገቢነትና ትክክለኛነታቸውን ወደ ሚያረጋግጠው የኦዲት ቡድን የሚመሩ ይሆናል። ትክክለኛነታቸው የተረጋገጠው ደግሞ በቦርዱ የአይሲቲ (ICT) ሲስተም ውስጥ ገብተው በቦርዱ እንዲጸድቁ ይደረጋልም ነው ያሉት። በማረጋገጥ ሂደቱ ላይ ያልተጣጣሙና ግድፈት ያለባቸው መረጃዎች ሲገኙ የኦዲት ቡድኑ በሚገባ ከመረመረ በኋላ ለውሳኔ የሚያቀርብ ሲሆን፤ ቦርዱም እነዚህን ጥብቅ የአሠራር ሂደቶች በሙሉ ተከትሎ የመጨረሻውን ውጤት ይፋ ያደርጋል ብለዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የምርጫው አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ሥራዎችን ከነገ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ይገመግማል
Jun 11, 2026 354
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ግምገማ ከነገ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ማካሄድ ይጀምራል። የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የፓርቲው አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ስራዎችን በሚመለከት መግለጫ ሰጥተዋል። አቶ ጌቱ በመግለጫቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ከሌሊት እስከ ሌሊት በመሰለፍ ድምፁን በመስጠት ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ነው። በዚህም ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ሰላማዊና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ በማካሄድ ኢትዮጵያውያን በፅናት አዲስ ታሪክ ጽፈዋል ብለዋል። ብልፅግና ፓርቲ ግቦችን አስቀምጦ የምርጫ ቦርድን ህጎች፣ አዋጅና መመሪያዎች ተከትሎ፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በትብብር እና በፉክክር በመንቀሳቀስ ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ ለምርጫው ሰላማዊነትና ዴሞክራሲያዊነት የሚያስችሉ ስራዎች በቁርጠኝነት ሲሰራ መቆየቱን አብራርተዋል። ከቅድመ ምርጫ እስከ ምርጫው ዕለት የታየውን የአመራሮችና የአባላቱን የላቀ መናበብ፣ መቀናጀትና ቁርጠኝነት ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል አስፈላጊ ነው ብለዋል። የድህረ ምርጫ ሥራዎችን በስኬት በመፈፀምም የተጀመረውን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የብልጽግና ጉዞ ይበልጥ ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችን ጨምሮ በሁሉም ወረዳ የሚገኙ የብልፅግና ህብረት አመራሮች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተያዙ መንትያ ግቦችን ለማሳካት የተከናወኑ ስራዎችን በመገምገም በቀጣይ ተግባራት ላይ ተግባቦት መፈጠሩን ጠቅሰዋል። ከነገ ጀምሮም በክልሉ በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎች በጠቅላላ ምርጫው አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ስራዎች እንደሚገመገም ጠቁመው፤ በዚህም በክልሉ በገጠር እና በከተማ የሚገኙ የፓርቲው አባላት እንደሚሳተፉ ነው የገለፁት። በመድረኩ ላይ ፓርቲው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫና በምርጫው ወቅት የነበረውን አፈጻጸም እንደሚገመገም አብራርተዋል። ከዚህ በተጨማሪም በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። በሚካሄደው ግምገማ በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲው አባላት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑም ኃላፊው ጥሪ አስተላልፈዋል።
በሶማሌ ክልል በለውጡ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ኦብነግ የበኩሉን አስተዋጽኦ ያደርጋል
Jun 11, 2026 305
ጅግጅጋ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) በሶማሌ ክልል በለውጡ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ። የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ምክትል ሊቀመንበር አሕመድ ያሲን፤ ከለውጡ በፊት በሶማሌ ክልል በነበረው አግላይና ፍትሃዊነት በጎደለው የፖለቲካ ስርዓት ኦብነግ የጫካ ትግል ውስጥ እንደነበር አስታውሰዋል። በሀገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በተፈጠረው ምቹ የፖለቲካ ምህዳር የትጥቅ ትግሉን በመተው ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል። በዚህ የትግል ሂደት የሃሳብና የፖሊሲ ልዩነቶች እንደተጠበቁ መሆናቸውን አንስተው፤ በሀገር ሉአላዊነት፣ በብሄራዊ ጥቅምና በዜጎች ሰላምና ደህንነት ጉዳይ ላይ የተለየ አቋምና አመለካከት የለንም ሲሉ አስረድተዋል። በሶማሌ ክልል በለውጡ ዓመታት ለመጣው ዘላቂ ሰላም፣ የሚታዩና የሚጨበጡ የልማት ስራዎች ፓርቲያቸው አድናቆት እንዳለው አንስተው ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፓርቲያቸው የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በፓርቲው ስም ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር የባእድ ተልእኮ በመቀበል ለጥፋት የሚንቀሳቀሱ ባንዳዎች መኖራቸውን አስታውሰዋል። እንዲህ አይነት የጥፋት ተልእኮ አንግበው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች በኦብነግ ውስጥ ምንም አይነት ስፍራ እንደሌላቸው አንስተው በጋራ እንታገላቸዋለን ሲሉም ገልጸዋል። ኦብነግ በሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ በክልሉ ያለውን ጠንካራ የፖለቲካ ተሳትፎ ማሳየቱን ገልጸው በሰላማዊ ትግል ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሂደት የበኩሉን መወጣቱን ይቀጥላል ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ሃይሎች በለውጡ የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር በአግባቡ በመጠቀም ለሀገር ጥቅምና ለሁለንተናዊ እድገት አጋዥና ደጋፊ በመሆን መስራት ይጠበቅብናል ሲሉም ተናግረዋል።
ጽንፈኛ ቡድኑ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይሳካ ያደረገው ሙከራ በሰላም ወዳዱ ሕዝብ ህልም ሆኖ ቀርቷል-አቶ ጣሂር መሀመድ
Jun 11, 2026 719
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ ጽንፈኛ ቡድኑ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይሳካ ያደረገው ሙከራ በሰላም ወዳዱ ሕዝብ ህልም ሆኖ መቅረቱን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አባል አቶ ጣሂር መሀመድ ገለጹ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ተሳትፎ ጎልቶ የታየበት ስኬታማ ሆኖ ተጠናቋል። ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ታዛቢዎች ምርጫው ዲሞክራሲያዊ፣ አካታችና ምሳሌነቱ የሚጠቀስ መሆኑን እማኝነታቸውን ሰጥተዋል። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አባል አቶ ጣሂር መሀመድ በምርጫውና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። አቶ ጣሂር እንዳሉት፤ የአማራ ክልል ሕዝብ በነጻነት የራሱን መሪዎች እንዳይመርጥ ጽንፈኛው ቡድን ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ጭምር በመቀናጀት ምርጫውን የማደናቀፍ ተግባራት ላይ ተጠምዶ መቆየቱን አንስተዋል። ጽንፈኛው ቡድን መራጩን ሕዝብ በዚህ ምርጫ ትሳተፍና፣ ይሄን ታደርግና የሚሉ ዛቻና ማስፈራሪያዎች ጭምር በመጠቀም አደገኛ ቅስቀሳዎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ በመሰል እንቅስቃሴዎች ሕዝቡ ዋጋ ሲከፍል መቆየቱን ጠቅሰዋል። እንዲያም ሆኖ የአማራ ክልል ሕዝብ ጫናዎችን ተቋቁሞ ለሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ በመስጠት ምርጫውን እንዲሳካ አድርጓል ያሉት አቶ ጣሂር፤ ለዚህ በሳል ውሳኔ ሕዝቡ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል። በዚህ ሁሉ ጫና ውስጥ ሕዝቡ ወጥቼ እመርጣለሁ፤ የምፈልገው መደበኛ የሆነ የመንግሥት አስተዳደር ነው በሚል መርህ በመመራት ምርጫውን ማሳካቱ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም በተጻጻሪው የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን የአማራን ሕዝብ እንደማይገልጸው ማሳያ መሆኑንም አስረድተዋል። በሕዝቡ ድምጽ የሚመሰረተው መንግሥት ዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሰራ እንደሚገባ ያመላከተ ነው ያሉት አቶ ጣሂር፤ ሕዝቡ በሰላም ዙሪያ በሚሰሩ ሥራዎች ተባባሪና ቁርጠኛ መሆኑን ያሳየበት ምርጫ መሆኑንም አብራርተዋል። በአማራ ክልል የተካሄደው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የክልሉ የጸጥታ ኃይልና ሚሊሻዎች በየደረጃው ካሉ አመራር ጋር በቅንጅት ያከናወኑት ተግባር ጉልህ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል። ይሄ ውጤት ደግሞ በመንግሥት እና በመደበኛ ሥርዓት ሕዝቡ እንዲተማመን ያስቻለ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ጣሂር ገለጻ፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚጋፋ የኃይል አሰላለፍ ሕዝብንም ሀገርንም ዋጋ የሚያስከፍል በመሆኑ ሕዝቡ በዚህ ላይ ግንዛቤ ጨብጦ ለሰላምና ዴሞክራሲ ግንባታ የራሱን አሻራ እንዲያሳርፍ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ እየሰራ ነው። "ጥያቄዎች የሚመለሱት በኃይል ነው" የሚል አቋም ይዘው እየተንቀሳቀሱ ያሉ አካላት ሰላማዊ መንገድን በመምረጥ ችግሮች በውይይት የሚፈቱበት አውድ መፍጠር ላይ ሊሰሩ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። መንግሥት የሰላም ጥሪ አቅርቦ በሩን ክፍት ማድረጉ የሚበረታታ መሆኑን አመልክተው፤ ይሄ ሥራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን አረጋገጡ
Jun 10, 2026 2074
አዲስ አበባ፤ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና ናይጄሪያ ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ትስስራቸውን ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ቢያንካ ኦዱሜግዉ-ኦጁክዉ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ውይይት አድርገዋል። ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያና ናይጄሪያ እ.አ.አ ከ1960ዎቹ አንስቶ የዘለቀ የረጅም ጊዜ ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው።   ይህንን የቆየ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገርም በጋራ ጥቅሞች ላይ ያተኮረ ቀጣይነት ያለው ቅንጅትና ምክክር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የናይጄሪያዋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ቢያንካ ኦዱሜግዉ-ኦጁክዉ በበኩላቸው፥ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ለማሳደግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። ናይጄሪያ በተለያዩ የልማትና የፖለቲካ ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር ይበልጥ በቅርበት ለመስራት ያላትን ዝግጁነትም አምባሳደር ቢያንካ አረጋግጠዋል። በዚሁ የሁለትዮሽ ምክክር ላይ የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርያሥላሴ እና የናይጄሪያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እና የፍትህ ሚኒስትር ላቲፍ ኦላሱንካንሚ ፋግቤሚ የጋራ ስምምነት ተፈራርመዋል። ሚኒስትሮቹ የተፈራረሙት ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል የፍርደኞች ልውውጥ ወይም ማስተላለፍን (Transfer of Sentenced Persons) የተመለከተ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ እና በናይጄሪያ የፍትህ ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ ትብብሮች መሰረት የሚጥል የሕግ ማዕቀፍ እንደሚፈጥር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የሁለቱ ወገኖች ውይይት እና ስምምነት በኢትዮጵያና በናይጄሪያ መካከል ያለውን አጋርነት ይበልጥ እንደሚያሳድገውም ገልጿል።
አንድ ሺህ ስምንት የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል ገብቷል
Jun 10, 2026 1640
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የአንድ ሺህ ስምንት የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተመለከተ ዕለታዊ መግለጫ ሰጥቷል።   የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በመግለጫቸው፤ የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ስራ እየተከናወነ ነው። በዚህም ከአንድ ምርጫ ክልል ውጭ በሁሉም የምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ ተጠናቋል ብለዋል። በዚህም የአንድ ሺህ ስምንት የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ገልጸዋል። ከ501ዱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል ደርሰዋል፣ ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች ናቸው ብለዋል። ከዚህም በተጨማሪ በመጠለያ ጣቢያዎችና በመከላከያ ካምፖች ድምፅ አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ውጤት የማዳመር ሥራ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 10, 2026 1632
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት ስኬት በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን ማስፈን የሚያስችል ተምሳሌታዊ አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሀገር አቀፍና የክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ቀረጻ ግብዓት ማሰባሰቢያ የውይይት መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።   የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ ኮሚሽኑ ያከናወናቸውን ተግባራትና የእስካሁን ሂደቶችን በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ፣ የተሳታፊ ልየታና ዋናውን የምክክር ጉባኤ የማካሄድ ዝግጅት ስኬታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያንና ባለድርሻ አካላት በእስካሁኑ ሂደት የነበራቸው ንቁ ተሳትፎም ነጻና ገለልተኛ ሀገራዊ ምክክርን ማስተባበር የሚያስችል አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራውም በታላላቅ ህዝባዊ መድረኮች በቀጥታና በጥናት ለኮሚሽኑ ቀርበው የማሰባሰብ ሥራ በስፋት መከናወኑን አብራርተዋል። በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የነበረው የህዝብና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎም ለሚሰሩ ሥራዎች ጥልቅ መነሻ የሚሆኑ የሀገር ሃብቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። በዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ሃሳብ የሚሰጡና የሚሳተፉ ተወካዮች በሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የማስመረጥ ስራ 93 በመቶ መፈጸም እንደተቻለ አስገንዝበዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ አካታችነት፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎም ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወሳኝ ምዕራፍ መሰረት መጣሉን አንስተዋል። የዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረጻ ዝግጅት የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የእስካሁኑ ሂደት ጉልህ ተሳትፏቸውን እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የእስካሁኑ ሂደት አካታች፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊነትም ተምሳሌታዊ የምክክር አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ አስገንዝበዋል።
ፖለቲካ
ቦርዱ የምርጫ ውጤቶችን ይፋ የሚያደርግበትን የድህረ-ምርጫ ተግባራት ለጋዜጠኞች አስጎበኘ  
Jun 11, 2026 410
አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ውጤቶችን ይፋ የሚያደርግበትን የድህረ-ምርጫ ተግባራት ለጋዜጠኞች አስጎበኘ። የምርጫ ቦርድ ውጤት ማረጋገጫ ክፍል አስተባባሪ ዶክተር ሽመልስ ሲሳይ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በሁሉም ምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ የተጠናቀቀላቸው ሙሉ ሰነዶች በቀጥታ ወደ ዋናው የቦርዱ ውጤት መረከቢያ ክፍል ይገባሉ። በመቀጠልም በማረጋገጫ ክፍሉ ውስጥ እያንዳንዱ ዕጩ ያገኘው ድምፅ ዋጋ ካላቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች፣ እንዲሁም በዕለቱ በአካል ተገኝተው ከፈረሙ መራጮች ቁጥር ጋር የመጣጣሙ ጉዳይ በጥብቅ እንደሚፈተሽ ተናግረዋል።   አስተባባሪው ዶክተር ሽመልስ እንደገለጹት፤ ይህን የማጣራት ሂደት የሚያልፉ መረጃዎች ተገቢነትና ትክክለኛነታቸውን ወደ ሚያረጋግጠው የኦዲት ቡድን የሚመሩ ይሆናል። ትክክለኛነታቸው የተረጋገጠው ደግሞ በቦርዱ የአይሲቲ (ICT) ሲስተም ውስጥ ገብተው በቦርዱ እንዲጸድቁ ይደረጋልም ነው ያሉት። በማረጋገጥ ሂደቱ ላይ ያልተጣጣሙና ግድፈት ያለባቸው መረጃዎች ሲገኙ የኦዲት ቡድኑ በሚገባ ከመረመረ በኋላ ለውሳኔ የሚያቀርብ ሲሆን፤ ቦርዱም እነዚህን ጥብቅ የአሠራር ሂደቶች በሙሉ ተከትሎ የመጨረሻውን ውጤት ይፋ ያደርጋል ብለዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የምርጫው አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ሥራዎችን ከነገ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ይገመግማል
Jun 11, 2026 354
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ግምገማ ከነገ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ማካሄድ ይጀምራል። የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የፓርቲው አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ስራዎችን በሚመለከት መግለጫ ሰጥተዋል። አቶ ጌቱ በመግለጫቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ከሌሊት እስከ ሌሊት በመሰለፍ ድምፁን በመስጠት ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ነው። በዚህም ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ሰላማዊና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ በማካሄድ ኢትዮጵያውያን በፅናት አዲስ ታሪክ ጽፈዋል ብለዋል። ብልፅግና ፓርቲ ግቦችን አስቀምጦ የምርጫ ቦርድን ህጎች፣ አዋጅና መመሪያዎች ተከትሎ፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በትብብር እና በፉክክር በመንቀሳቀስ ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ ለምርጫው ሰላማዊነትና ዴሞክራሲያዊነት የሚያስችሉ ስራዎች በቁርጠኝነት ሲሰራ መቆየቱን አብራርተዋል። ከቅድመ ምርጫ እስከ ምርጫው ዕለት የታየውን የአመራሮችና የአባላቱን የላቀ መናበብ፣ መቀናጀትና ቁርጠኝነት ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል አስፈላጊ ነው ብለዋል። የድህረ ምርጫ ሥራዎችን በስኬት በመፈፀምም የተጀመረውን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የብልጽግና ጉዞ ይበልጥ ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችን ጨምሮ በሁሉም ወረዳ የሚገኙ የብልፅግና ህብረት አመራሮች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተያዙ መንትያ ግቦችን ለማሳካት የተከናወኑ ስራዎችን በመገምገም በቀጣይ ተግባራት ላይ ተግባቦት መፈጠሩን ጠቅሰዋል። ከነገ ጀምሮም በክልሉ በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎች በጠቅላላ ምርጫው አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ስራዎች እንደሚገመገም ጠቁመው፤ በዚህም በክልሉ በገጠር እና በከተማ የሚገኙ የፓርቲው አባላት እንደሚሳተፉ ነው የገለፁት። በመድረኩ ላይ ፓርቲው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫና በምርጫው ወቅት የነበረውን አፈጻጸም እንደሚገመገም አብራርተዋል። ከዚህ በተጨማሪም በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። በሚካሄደው ግምገማ በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲው አባላት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑም ኃላፊው ጥሪ አስተላልፈዋል።
በሶማሌ ክልል በለውጡ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ኦብነግ የበኩሉን አስተዋጽኦ ያደርጋል
Jun 11, 2026 305
ጅግጅጋ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) በሶማሌ ክልል በለውጡ ዓመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ። የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ምክትል ሊቀመንበር አሕመድ ያሲን፤ ከለውጡ በፊት በሶማሌ ክልል በነበረው አግላይና ፍትሃዊነት በጎደለው የፖለቲካ ስርዓት ኦብነግ የጫካ ትግል ውስጥ እንደነበር አስታውሰዋል። በሀገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በተፈጠረው ምቹ የፖለቲካ ምህዳር የትጥቅ ትግሉን በመተው ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል። በዚህ የትግል ሂደት የሃሳብና የፖሊሲ ልዩነቶች እንደተጠበቁ መሆናቸውን አንስተው፤ በሀገር ሉአላዊነት፣ በብሄራዊ ጥቅምና በዜጎች ሰላምና ደህንነት ጉዳይ ላይ የተለየ አቋምና አመለካከት የለንም ሲሉ አስረድተዋል። በሶማሌ ክልል በለውጡ ዓመታት ለመጣው ዘላቂ ሰላም፣ የሚታዩና የሚጨበጡ የልማት ስራዎች ፓርቲያቸው አድናቆት እንዳለው አንስተው ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፓርቲያቸው የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በፓርቲው ስም ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር የባእድ ተልእኮ በመቀበል ለጥፋት የሚንቀሳቀሱ ባንዳዎች መኖራቸውን አስታውሰዋል። እንዲህ አይነት የጥፋት ተልእኮ አንግበው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች በኦብነግ ውስጥ ምንም አይነት ስፍራ እንደሌላቸው አንስተው በጋራ እንታገላቸዋለን ሲሉም ገልጸዋል። ኦብነግ በሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ በክልሉ ያለውን ጠንካራ የፖለቲካ ተሳትፎ ማሳየቱን ገልጸው በሰላማዊ ትግል ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሂደት የበኩሉን መወጣቱን ይቀጥላል ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ሃይሎች በለውጡ የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር በአግባቡ በመጠቀም ለሀገር ጥቅምና ለሁለንተናዊ እድገት አጋዥና ደጋፊ በመሆን መስራት ይጠበቅብናል ሲሉም ተናግረዋል።
ጽንፈኛ ቡድኑ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይሳካ ያደረገው ሙከራ በሰላም ወዳዱ ሕዝብ ህልም ሆኖ ቀርቷል-አቶ ጣሂር መሀመድ
Jun 11, 2026 719
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ ጽንፈኛ ቡድኑ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይሳካ ያደረገው ሙከራ በሰላም ወዳዱ ሕዝብ ህልም ሆኖ መቅረቱን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አባል አቶ ጣሂር መሀመድ ገለጹ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ተሳትፎ ጎልቶ የታየበት ስኬታማ ሆኖ ተጠናቋል። ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ታዛቢዎች ምርጫው ዲሞክራሲያዊ፣ አካታችና ምሳሌነቱ የሚጠቀስ መሆኑን እማኝነታቸውን ሰጥተዋል። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አባል አቶ ጣሂር መሀመድ በምርጫውና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። አቶ ጣሂር እንዳሉት፤ የአማራ ክልል ሕዝብ በነጻነት የራሱን መሪዎች እንዳይመርጥ ጽንፈኛው ቡድን ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ጭምር በመቀናጀት ምርጫውን የማደናቀፍ ተግባራት ላይ ተጠምዶ መቆየቱን አንስተዋል። ጽንፈኛው ቡድን መራጩን ሕዝብ በዚህ ምርጫ ትሳተፍና፣ ይሄን ታደርግና የሚሉ ዛቻና ማስፈራሪያዎች ጭምር በመጠቀም አደገኛ ቅስቀሳዎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ በመሰል እንቅስቃሴዎች ሕዝቡ ዋጋ ሲከፍል መቆየቱን ጠቅሰዋል። እንዲያም ሆኖ የአማራ ክልል ሕዝብ ጫናዎችን ተቋቁሞ ለሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ በመስጠት ምርጫውን እንዲሳካ አድርጓል ያሉት አቶ ጣሂር፤ ለዚህ በሳል ውሳኔ ሕዝቡ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል። በዚህ ሁሉ ጫና ውስጥ ሕዝቡ ወጥቼ እመርጣለሁ፤ የምፈልገው መደበኛ የሆነ የመንግሥት አስተዳደር ነው በሚል መርህ በመመራት ምርጫውን ማሳካቱ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም በተጻጻሪው የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን የአማራን ሕዝብ እንደማይገልጸው ማሳያ መሆኑንም አስረድተዋል። በሕዝቡ ድምጽ የሚመሰረተው መንግሥት ዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሰራ እንደሚገባ ያመላከተ ነው ያሉት አቶ ጣሂር፤ ሕዝቡ በሰላም ዙሪያ በሚሰሩ ሥራዎች ተባባሪና ቁርጠኛ መሆኑን ያሳየበት ምርጫ መሆኑንም አብራርተዋል። በአማራ ክልል የተካሄደው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የክልሉ የጸጥታ ኃይልና ሚሊሻዎች በየደረጃው ካሉ አመራር ጋር በቅንጅት ያከናወኑት ተግባር ጉልህ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል። ይሄ ውጤት ደግሞ በመንግሥት እና በመደበኛ ሥርዓት ሕዝቡ እንዲተማመን ያስቻለ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ጣሂር ገለጻ፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚጋፋ የኃይል አሰላለፍ ሕዝብንም ሀገርንም ዋጋ የሚያስከፍል በመሆኑ ሕዝቡ በዚህ ላይ ግንዛቤ ጨብጦ ለሰላምና ዴሞክራሲ ግንባታ የራሱን አሻራ እንዲያሳርፍ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ እየሰራ ነው። "ጥያቄዎች የሚመለሱት በኃይል ነው" የሚል አቋም ይዘው እየተንቀሳቀሱ ያሉ አካላት ሰላማዊ መንገድን በመምረጥ ችግሮች በውይይት የሚፈቱበት አውድ መፍጠር ላይ ሊሰሩ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። መንግሥት የሰላም ጥሪ አቅርቦ በሩን ክፍት ማድረጉ የሚበረታታ መሆኑን አመልክተው፤ ይሄ ሥራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን አረጋገጡ
Jun 10, 2026 2074
አዲስ አበባ፤ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና ናይጄሪያ ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ትስስራቸውን ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ቢያንካ ኦዱሜግዉ-ኦጁክዉ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ውይይት አድርገዋል። ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያና ናይጄሪያ እ.አ.አ ከ1960ዎቹ አንስቶ የዘለቀ የረጅም ጊዜ ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው።   ይህንን የቆየ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገርም በጋራ ጥቅሞች ላይ ያተኮረ ቀጣይነት ያለው ቅንጅትና ምክክር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የናይጄሪያዋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ቢያንካ ኦዱሜግዉ-ኦጁክዉ በበኩላቸው፥ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ለማሳደግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። ናይጄሪያ በተለያዩ የልማትና የፖለቲካ ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር ይበልጥ በቅርበት ለመስራት ያላትን ዝግጁነትም አምባሳደር ቢያንካ አረጋግጠዋል። በዚሁ የሁለትዮሽ ምክክር ላይ የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርያሥላሴ እና የናይጄሪያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እና የፍትህ ሚኒስትር ላቲፍ ኦላሱንካንሚ ፋግቤሚ የጋራ ስምምነት ተፈራርመዋል። ሚኒስትሮቹ የተፈራረሙት ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል የፍርደኞች ልውውጥ ወይም ማስተላለፍን (Transfer of Sentenced Persons) የተመለከተ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ እና በናይጄሪያ የፍትህ ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ ትብብሮች መሰረት የሚጥል የሕግ ማዕቀፍ እንደሚፈጥር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የሁለቱ ወገኖች ውይይት እና ስምምነት በኢትዮጵያና በናይጄሪያ መካከል ያለውን አጋርነት ይበልጥ እንደሚያሳድገውም ገልጿል።
አንድ ሺህ ስምንት የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል ገብቷል
Jun 10, 2026 1640
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የአንድ ሺህ ስምንት የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተመለከተ ዕለታዊ መግለጫ ሰጥቷል።   የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በመግለጫቸው፤ የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ስራ እየተከናወነ ነው። በዚህም ከአንድ ምርጫ ክልል ውጭ በሁሉም የምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ ተጠናቋል ብለዋል። በዚህም የአንድ ሺህ ስምንት የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ገልጸዋል። ከ501ዱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል ደርሰዋል፣ ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች ናቸው ብለዋል። ከዚህም በተጨማሪ በመጠለያ ጣቢያዎችና በመከላከያ ካምፖች ድምፅ አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ውጤት የማዳመር ሥራ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 10, 2026 1632
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት ስኬት በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን ማስፈን የሚያስችል ተምሳሌታዊ አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሀገር አቀፍና የክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ቀረጻ ግብዓት ማሰባሰቢያ የውይይት መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።   የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ ኮሚሽኑ ያከናወናቸውን ተግባራትና የእስካሁን ሂደቶችን በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ፣ የተሳታፊ ልየታና ዋናውን የምክክር ጉባኤ የማካሄድ ዝግጅት ስኬታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያንና ባለድርሻ አካላት በእስካሁኑ ሂደት የነበራቸው ንቁ ተሳትፎም ነጻና ገለልተኛ ሀገራዊ ምክክርን ማስተባበር የሚያስችል አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራውም በታላላቅ ህዝባዊ መድረኮች በቀጥታና በጥናት ለኮሚሽኑ ቀርበው የማሰባሰብ ሥራ በስፋት መከናወኑን አብራርተዋል። በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የነበረው የህዝብና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎም ለሚሰሩ ሥራዎች ጥልቅ መነሻ የሚሆኑ የሀገር ሃብቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። በዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ሃሳብ የሚሰጡና የሚሳተፉ ተወካዮች በሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የማስመረጥ ስራ 93 በመቶ መፈጸም እንደተቻለ አስገንዝበዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ አካታችነት፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎም ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወሳኝ ምዕራፍ መሰረት መጣሉን አንስተዋል። የዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረጻ ዝግጅት የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የእስካሁኑ ሂደት ጉልህ ተሳትፏቸውን እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የእስካሁኑ ሂደት አካታች፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊነትም ተምሳሌታዊ የምክክር አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ አስገንዝበዋል።
ማህበራዊ
በክልሉ ተማሪዎች በክልል አቀፍ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆኑ የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል
Jun 11, 2026 336
ወራቤ ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በክልል የተማሪዎችን ብቃትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ በክልል አቀፍ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆኑ መሰራቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ ክልላዊ የፈተና ዝግጅትን በማስመልከት ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በክልሉ አዲሱን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ የተማሪዎችን ብቃትና ተወዳዳሪነት ማሳደግ ተችሏል። የተማሪዎችን ብቃትና ተወዳዳሪነት ለመለካት ዘንድሮ በሚሰጠው የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናም ከ183 ሺህ 790 በላይ ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ተናግረዋል። በክልል ደረጃ የሚሰጠውን ፈተና ውጤታማ ለማድረግ ተማሪዎች በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ሲሰራ መቆየቱንም ነው አቶ አንተነህ የገለጹት። ለዚህም ከመደበኛ የመማር ማስተማር ሥራው በተጨማሪ በማጠናከሪያ ትምህርት ተማሪዎችን የማብቃት ሥራ ተከናውኗል ብለዋል። ተማሪዎች ኩረጃን በመጸየፍ የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲያመጡ በስነልቦና የተሰራው ስራም ውጤት እያስገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን በተገቢው ለመምራትም 139 በላይ ፈታኝ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮችና ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የመፈተኛ ማዕከላት መዘጋጀታቸውን ነውያስታወቁት። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አያይዘውም 3ኛው ዙር ክልል አቀፍ የሳይንስና ፈጠራ ሥራዎች አውደ ርዕይና ኤግዚቢሽን ነገ በቡታጅራ ከተማ እንደሚካሄድ አመልክተዋል። በኤግዚቢሽኑ በተማሪዎች፣ በመምህራን፣ በግል ፈጠራ ባለቤቶች እና በፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የተሰሩ የፈጠራ ሥራዎች ለውድድር እንደሚቀርቡም ገልጸዋል። የማህበረሰቡን ችግር ለሚፈቱ የፈጠራ ሥራዎች የገበያ ትስስር ከማመቻቸት ባለፈ ማበረታቻና እውቅና እንደሚሰጥም ተናግረዋል። በክልሉ የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ታውቋል።  
የጤና ነገር
Jun 11, 2026 222
በዮሐንስ ደርበው ቶሎ ምልክት የማያሳየው፤ ምልክቶቹ ከታዩ በኋላም ወዲያው ካልታከመ ለአዕምሮ ዕድገት ውስንነት የሚዳርገው በሽታ … በዓለም አቀፍ ደረጃ የተካሄዱ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከሚወለዱ 2 ሺህ ሕጻናት መካከል አንዱ የታይሮይድ ሆርሞን ሳይኖረው ይወለዳል። ለመሆኑ የታይሮይድ ሆርሞን አስፈላጊነት ምን ያህል ነው? ባይኖርስ ምን ይከሰታል? በወቅቱ ካልታከመ እስከ አዕምሮ ህመም የሚያደርሰው የታይሮድ ሆርሞን እጥረት (አለመኖር) በሚያስከትላቸው ችግሮችና ቀድመው ሊደረጉ በሚገባቸው ጥንቃቄዎች ላይ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የሕጻናት፣ የስኳር ህመም እና የሆርሞን ችግሮች ሰብስፔሻሊስት ዶክተር ፍቅር መሠረት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። · የታይሮይድ ሆርሞን ምንድን ነው? እንደባለሙያዋ ገለጻ፤ የታይሮይድ ሆርሞን ታይሮይድ ዕጢ ከሚባለው የአካል ክፍል የሚመነጭ ሆርሞን ነው። በሰውነታችን ውስጥም እጅግ አስፈላጊ ከምንላቸው ሆርሞኖች አንዱ ነው ይላሉ። ጠቃሚነቱን ሲያስረዱም፤ በተለይም ሕጻናት ላይ ለአዕምሮ ዕድገት፣ ለሰውነት ዕድገት እንዲሁም እያንዳንዱ ኅዋሳችን የታይሮይድ ሆርሞንን ለሜታቦሊዝም (ሰውነታችን ኃይል ማመንጨት እንዲችል) ይጠቀምበታል ብለዋል። · የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት መንስዔዎች መንስዔዎቹን በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ጠቁመው፤ አንደኛው ሲወለዱ ጀምሮ የሚከሰት የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት ሲሆን ሁለተኛው ልጆች ካደጉ በኋላ በማንኛውም የዕድሜ ክልል የሚከሰት መሆኑን አብራርተዋል። አንደኛው፤ ሕጻናት ሲወለዱ ጀምሮ የታይሮድ ሆርሞን እጥረት የሚከሰትበት አጋጣሚ መኖሩን ጠቅሰው፤ ለዚህም ከሚነሱት ምክንያቶች አንዱ የታይሮይድ ዕጢ አለመፈጠር መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም ጽንስ በማሕጸን ውስጥ ሆኖ ዕድገቱ ቀጥሎ ሳለ፤ በአንጻሩ የታይሮይድ ዕጢ በአግባቡ ሳያድግ ይቀርና የሚፈለገውን ሆርሞን እንዳያመነጭ የሚሆንበት አጋጣሚ ይኖራል ብለዋል። አክለውም፤ ዕጢው መቀመጥ ባለበት ተገቢ ቦታ ላይ በትክክል ሳይቀመጥ ሲቀር በሆርሞን ማመንጨት ላይ ችግሮች እንደሚስተዋሉ አመላክተዋል። በሌላ በኩል የታይሮይድ ዕጢ የተለያዩ የዕድገት ደረጃዎችን አልፎ ሆርሞን እንደሚያመነጭ ገልጸው፤ በአንዱ ደረጃ ላይ ዕክል ቢያጋጥመው ሆርሞን ማመንጭት እንደማይችል አስረድተዋል። ሁለተኛው፤ ልጆች ካደጉ በኋላ ለሚከሰተው የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት (አኳየርድ) ደግሞ ምክንያቱ፤ የታይሮይድ ዕጢ በነጭ የደም ኅዋሶች ሲጎዳ መሆኑን አስረድተዋል። · በታይሮይድ ዕጢ ላይ የሚከሰቱ ችግሮች የተለያየ ዓይነት የታይሮይድ ዕጢ ችግር ሊኖር እንደሚችል የገልጹት ዶክተር ፍቅር፤ የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት፣ የታይሮይድ ሆርሞን መብዛት፣ የታይሮይድ ዕጢ ማደግ (ጎይተር)፣ የታይሮይድ ሆርሞን ካንሰር የሚሉትን ለአብነት ጠቅሰዋል። በአብዛኛው በሕጻናት ላይ የሚያጋጥመው የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት መሆኑንም በማስረዳት። · የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት በሕጻናትና በአዋቂዎች የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት በሕጻናት (ኮንጅናይታል የሚባለው ኬዝ) እና በአዋቂዎች (አኳየርድ የሚባለው ኬዝ) ዘንድ እንደሚከሰት ዶክተር ፍቅር አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት በሕጻናት ላይ በአብዛኛው የሚከሰተውም፤ ሲፈጠሩ ጀምሮ የዕጢው አለመኖር፣ የዕጢው በትክክለኛ ቦታው ያለመቀመጥ መሆኑን አስረድተዋል። በአዋቂዎች ዘንድ የሚከሰተው ደግሞ በአዮዲን እጥረት እንዲሁም የታይሮድ ዕጢ በነጭ የደም ኅዋሶች መጎዳት ምክንያት መሆኑን አንስተዋል። · የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት ምልክቶች ምንድን ናቸው? ኬዙ ያለባቸው ሕጻናትንስ መቼ ወደ ሕክምና ተቋም ይሂዱ? የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት ሲኖር እንደሌሎች በሽታዎች አጣዳፊ ምልክቶች እንደሌሉት የሚገልጹት ዶክተር ፍቅር፤ ምልክቶቹ ቀስ በቀስ የሚመጡ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለምሳሌ፡- የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት ኖሯቸው ከሚወለዱ ሕጻናት መካከል አብዛኞቹ በመጀመሪያዎቹ አንድ/ሁለት ሳምንት ምልክት ላያሳዩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ይህም በመሆኑ በተለያዩ ሀገራት የሕጻናት ቅድመ ምርመራ እንደሚደረግ አመላክተዋል። ምክንያቱም የታይሮይድ ሆርሞን እጥረትን ቀድሞ ማወቅ መከላከል የሚያስችለው የጎንዮሽ ጉዳት ስላለ ነው ይላሉ። በሕጻናት ላይ በመጀመሪያው ወራቸው ከሚታዩ ምልክቶች መካከልም፤ ረጅም ሠዓት መተኛት፣ ጡት የመጥባት ፍላጎት አለመኖር፣ የሰገራ መድረቅ፣ በአንዳንድ ልጆች ላይ የፊት፣ የሆድ አካባቢ፣ ዕጅና እግር ማበጥ፣ ከሁለት ሳምንት በላይ የሚቆይ የቆዳ ቢጫ መሆን የሚሉት እንደሚገኙበት አብራርተዋል። ይህን ተከትሎ በወቅቱ ወደ ሕክምና መውሰድ ካልተቻለ ግን ይላሉ፤ የዕድገት መዘግየት ምልክት እንደሚታይ አስረድተዋል። መቀመጥ፣ መቆም፣ መራመድ፣ መናገር፣ … የሚሉትን ጨምሮ ከዕድሜ ክልላቸው እና ከሚጠበቅባቸው አንጻር ካነሱ (ዕድገታቸው በሁሉም መንገድ ወደ ኋላ ከቀረ) የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት እንዳለመ መገንዘብ ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም፤ የቆዳ መድረቅ፣ የፀጉር መነቃቀል፣ ቀልጣፋ አለመሆን (መፍዘዝ)፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ እና ከዕድሜ አንጻር የቁመት ማጠር ዋና ዋና ምልክቶቹ መሆናቸውን ነው ያስረዱት። · አሳሳቢነት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተካሄዱ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት፤ ከሚወለዱ 2 ሺህ ሕጻናት መካከል አንዱ የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት ይኖርበታል። እንደ ዓለም በአጠቃላይ ካሉ ሕጻናትም ከ 1 እስከ 2 በመቶ ያህሉ የታይሮድ ሆርሞን እጥረት ተጠቂ መሆናቸውን አንስተዋል። · ምክረ ሐሳብ በማኅበረሰብ ደረጃ በልጆች ላይ ያልተለመደ (የተለየ) ምልክት ሲታይ ሁሌም የሕክምና ባለሙያ ማማከር አስፈላጊ መሆኑን መክረዋል። የታይሮይድ ሆርሞን እጥረትን ቀድሞ አለማወቅ (በተለይም እስከ 5 ዓመታቸው ድረስ ታውቆ ሕክምና ካልተጀመረ) የአዕምሮ ዕድገት ውስንነት እንደሚያስከትል የገለጹት የሕክምና ባለሙያዋ፤ ወላጆች፣ አሳዳጊዎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መክረዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ልንከላከላቸው ከምንችላቸው የአዕምሮ ዝግመት መንስዔዎች መካከል የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት አንዱ መሆኑን ገልጸው፤ በተለያዩ ሀገራት የሕጻናት ቅድመ ምርመራ የሚሠራው ለዚሁ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ጎበዝ ተማሪ ሆነው ውጤታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ከሆነ፣ የቁመት ማጠር ካለ፣ የሰገራ መድረቅ ካለ፣ ለመጫዎት እና ለመመገብ ፍላጎት ካላሳዩ፣ የቆዳ ድርቀት፣ የጸጉር መነቃቀል ሲኖር የታይሮድ ሆርሞን እጥረት ሊሆን ስለሚችል አስፈላጊውን ምርመራ ማድረግን መክረዋል። የታይሮይድ ሆርሞን እጥረት በቀላሉ ሙሉ በሙሉ መታከም ይችላል፤ ነገርግን ዛሬ ነገ በሚል መዘናጋት እና ምልክቶችን ባለማስተዋል በሽታው ወደ ሌላ ህመም የመሸጋገር ዕድል ስለሚኖረው ሕክምናውም በዚያው ልክ ውድ እንደሚሆን አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ዩኒቨርሲቲው የ''ጀፎረ''ን ማህበረሰባዊ እሴት በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናትና ምርምር ሰነድ አቀረበ
Jun 11, 2026 269
ወልቂጤ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ''ጀፎረ''ን ማህበረሰባዊ እሴት በዓለም አቀፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናትና ምርምር ሰነድ ማቅረቡን አስታወቀ። ዩኒቨርሲቲው የጉራጌ ማህበራዊ እና ባህላዊ መንደር ''ጀፎረ''ን ለማህበራዊና ለኢኮኖሚያዊ እድገት ያለውን አበርክቶና በቅርስነት ለማስመዝገብ በሚያስችል የጥናት ሰነድ ላይ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ተካሄዷል።   ''ጀፎረ'' በጉራጌ ማህበረሰብ ባህልና አሰፋፈር ውስጥ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው፣ በየመንደሩ መሃል የሚገኝ ሰፊ፣ ሳር የለበሰ የጋራ አደባባይ ወይም ጎዳና ነው። ይህ ቦታ ተራ የከተማ መንገድ ሳይሆን፣ በሁለቱም በኩል ያሉ መኖሪያ ቤቶችና የውጪው አጥር የሚገናኙበት የባህል ማዕከል ነው። ''ጀፎረ'' በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ክብር ያለውና በጥንቃቄ የሚጠበቅ በመሆኑ፣ እንደ ሰብል ማልማት ወይም የግል ህንፃ መገንባት ያሉ ስራዎች ጨርሶ አይፈቀዱበትም። በአጠቃላይ ጀፎረ የአንድነት፣ የሰላምና የማህበረሰባዊ መስተጋብር ምልክት ሆኖ ያገለግላል። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት አብድልሙህሲን ሃሰን (ዶ/ር) በውይይቱ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ተግባራትን እያከናወነ ነው።   የዚሁ አካል የሆነው "ጀፎረ" የዳኝነት እና የእርቅ ስፍራ፣ የበዓላት እና የክዋኔ ማዕከል፣ የምክክርና የደቦ ማህበረሰባዊ እሴትን በዓለም አቀፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ የሚያስችል ጥናትና ምርምር በማካሄድ ለሚመለከተው አካል ማቅረቡን አስረድተዋል። ጥናታዊ ፅሁፉን ያቀረቡት መምህር መለሰ ሟረታ "ጀፎረ" ከሚሰጠው ማህበረሰባዊ እና ሃገራዊ ጠቀሜታ ባለፈ ለቱሪዝም መዳረሻነት ወሳኝ ቦታ መሆኑን አንስተዋል። ከጉዳት በመጠበቅ ለትውልድ እንዲተላለፍ እየተተገበሩ ያሉ ማህበረሰባዊ ደንቦች በአግባቡ እንዲደራጁ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲው እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደግነህ ቦጋለ በበኩላቸው፤ የጀፎረ ማህበረሰባዊ እሴትን ለማልማት እና ለማስተዋወቅ ቢሮው በጥናት አስደግፎ እየሰራ ነው ብለዋል።   በዚህም ሀገር በቀል እውቀትን ወደ ተግባር በማምጣት የገጠሩ ማህበረሰብን ኑሮ ለማሻሻል እንዲሁም ከገጠር ኮሪደር ልማት ጋር በማስተሳሰር ምቹ የቱሪዝም ምህዳር የመፍጠር ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። ''ጀፎረ'' ባህላዊና ሀይማኖታዊ በዓላት የሚከበሩበትና የዕርቅ ስርዓት የሚፈፀምበት ስፍራ፣ ጽዳቱ የተጠበቀና የዘመናዊ አኗኗር እሳቤ ማሳያ ነው ያሉት የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመርጋ ናቸው፡፡   ከዚህም ባለፈ ለቱሪዝም መዳረሻ ቦታ እየሆነ መምጣቱን ጠቁመው ማህበረሰባዊ እሴቱን እና ተፈጥሯዊ ይዘቱን ሳይለቅ ተጠብቆ እንዲቆይ ከመቼውም ጊዜ በላይ እየተሰራ እንደሆነም አብራርተዋል። የጉራጌ የጆካ ባህላዊ ሸንጎ ሰብሳቢ አቶ በለጠ ወልዴ በበኩላቸው ''ጀፎረ'' ሁሉም በጋራ የሚገለገልበት፣ ፍትህ የሚሰጥበት፣ ደስታና ሃዘን የመሰሉ ማህበራዊ መስተጋብሮች የሚከወኑበት፣ አባቶች ባህላዊ የዳኝነት ስርዓት የሚሰጡበት የማህበረሰብ የወል ሀብት መሆኑን ተናግረዋል።   በውይይት መድረኩ ላይም የአካባቢው ማህበረሰብ ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የክልሉና የዞን ባህልና ቱሪዝም ዘርፍ አመራሮች ተገኝተዋል።
በሳዑዲ አረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ 1655 ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ ምህረት ተደረገላቸው
Jun 11, 2026 307
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በሳዑዲ አረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ 1655 ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ እንዲሰጣቸው መደረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። ኢትዮጵያውያኑ ምህረት የተደረገላቸው ሚኒስቴሩ ሪያድ የሚገኘውን ሚሲዮን እና በጅዳ ያለውን ቆንስላ ጽህፈት ቤት በማስተባበር ባደረገው የዲፕሎማሲ ጥረት መሆኑን አመልክቷል። ይህ ውጤት መንግሥት በውጭ ግንኙነቱ ለዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በሰጠው ትኩረት የተገኘ መሆኑን ገልጿል። መንግሥት ከዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ አኳያ በሳዑዲ አረቢያ ቀሪ የዲፕሎማሲ ጥረት የሚሹ ጉዳዮችን በተመለከተም ክትትል እያደረገ ይገኛል። በዚሁ አጋጣሚ መንግሥት ሕብረተሰቡ ከሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች በማኅበራዊ ሚዲያ የታጀበ ሀሰተኛ ማታለያ ድርጊት የውጭ አገር ጉዞ ራሱን እንዲጠብቅ እያሳሰበ፤ ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን የሕግ ተጠያቂ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቋል።
ኢኮኖሚ
ኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው
Jun 11, 2026 313
ወላይታ ሶዶ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የደቡብ ማዕከል አስታወቀ። ማዕከሉ በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በግብርና ልማት ሥራ የተሰማሩ ኩባንያዎች ተግባራት አፈጻጸምን የሚገመግም መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል።   በኢንስቲትዩቱ የደቡብ ማዕከል የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ዳይሬክተር አቶ ተሰማ ህርባዬ እንዳሉት፤ አርሶ አደሮችን በኩታ ገጠም ግብርና ቢዝነስ ኩባንያዎች በማደራጀት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየተሰራ ነው። ለዚህም ማዕከሉ በተመረጡ ወረዳዎች በኩታ ገጠም እርሻ አርሶ አደሮችን በማደራጀት ምርታማነታቸው እንዲያድግና የገበያ ትስስር እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ኩታ ገጠም እርሻ አርሶ አደሩ የግብአት አቅርቦትን በቀላሉ የሚያገኝበት አውድ ከመፍጠሩ ባለፈ የሜካናይዝድ እርሻን በመተግበር ምርትና ምርታማነቱን ለማሳደግ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል። ኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አድማሱ አወቀ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በክልሉ ግብርናን በማዘመን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ ነው።   ለዚህም ቢሮው ከግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሮች እያደረሰ ይገኛል ብለዋል። ይህም አርሶ አደሩ የግብርና ምርቶቹን በጥራትና በብዛት ለገበያ በማቅረብ ተወዳዳሪ እንደሚያደርገው ነው የተናገሩት። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን የቸሃ ወረዳ ግብርና ቢዝነስ ኩባንያ አባል አርሶ አደር አብዱራሃማን ሙክታር፤ ከዚህ ቀደም በተናጠል ባከናወኑት የእርሻ ስራ ብዙም ሳይጠቀሙ ቆይተዋል።   በአሁኑ ወቅት በኩታ ገጠም እርሻ ተደራጅተው ኩባንያ ከፈጠሩ ወዲህ ጉልበታቸውን በማስተባበር እንዲሁም ግብአትና ቴክኖሎጂ በመጠቀም ምርታማነታቸውን እንዳሳደጉ ተናግረዋል። ይህም ምርታቸውን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ የተሻለ ገቢ በማግኘት የቤተሰባቸውን ኑሮ ለማሻሻል እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። በስልጤ ዞን የሳንኩራ ወረዳ ግብርና ቢዝነስ ኩባንያ አባል ወይዘሮ አሚና ሃጂ ጀማል በበኩላቸው፤ 85 ወንዶች እና 15 ሴቶች በግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ተደራጅተው የጓሮ አትክልትና ሌሎች ምርቶች እያመረቱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።   በዚህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚ እየሆኑ ከመምጣታቸው ባለፈ ገበያን በማረጋጋት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከማዕከላዊ እና ከሲዳማ ክልሎች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በክልሉ የግብርና ግብዓትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል
Jun 11, 2026 253
ሃዋሳ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል የግብርና ግብዓት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። በክልሉ በዘንድሮው የመኸር ወቅት ከ169 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡ የሲዳማ ክልል የዘንድሮ መኸር እርሻ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እንደተናገሩት በክልሉ በግብርና ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ገበያን ለማረጋጋት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በተያዘው የመኸር ወቅትም የግብርና ግብዓትና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራም አስገንዝበዋል። በዚህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ገበያን ለማረጋጋት የሚያስችል ትርፍ ምርት እንዲመረት አመራሩ ድጋፍና ክትትሉን ማጠናከር አለበት ሲሉም አክለዋል። የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው እንዳሉት በክልሉ በዘንድሮ የመኸር ወቅት ከ169 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በማልማት ከ16 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል።   በምርት ዘመኑ የማሳ ሽፋንን ለማሳደግ እና ምርታማነትን ለሚጨምሩ ግብዓትና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት እንደሚሰጥ የጋራ መግባባት ላይ መደረሱንም ተናግረዋል። ለግብርና ሥራው ከማሳ ዝግጅት ጀምሮ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦት በበቂ ሁኔታ መኖሩን አቶ መምሩ ገልጸው፣ በዓመቱ በክልሉ ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ እስካሁን ድረስ ከ75 ከመቶ በላይ የሚሆነውን ለማሳካት ተችሏል ብለዋል። በመኸር እርሻው የግብርና ግብዓትና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ለውጥ በማምጣት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል። የዛሬው መድረክ በምርት ዘመኑ ለተያዘው ዕቅድ ስኬታማነት አመራሩ የጋራ መግባባት ላይ እንዲደርስ ማድረጉን የተናገሩት ደግሞ የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርናና ገጠር ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ዱሬሳ ሌዳሞ ናቸው፡፡   በዞኑ በዘንድሮ የመኸር ወቅት ከ43 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ4 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም ተናግረዋል። ለዚህም የቴክኖሎጂና የግብዓት አጠቃቀም ላይ ለውጥ በማምጣት ምርትና ምርታማነትን የማሳደግ ሥራ ይሰራል ብለዋል፡፡ በንቅናቄ መድረኩ ላይ በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን ለዘንድሮ የመኸር እርሻ ልማት የተዘጋጁ ሰነዶችም ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በሁሉም የኢኮኖሚ አመላካቾች የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ታሳቢ ያደረገ ነው
Jun 11, 2026 418
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በሁሉም የኢኮኖሚ አመላካቾች የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ፡፡ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 25ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት የበጀት መግለጫ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡   ምክር ቤቱም በቀረበው የ2019 የበጀት መግለጫ ላይ ከተወያየ በኋላ ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ መርቶታል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ለምክር ቤት ባቀረቡት የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ እንደገለጹት፤ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውና የአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ ትግበራ ስኬታማ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጣዊና ውጫዊ ጫናዎችን በብቃት በመቋቋም ጠንካራ አፈጻጸም ማስመዝገቡን ገልጸው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው አበርክቶ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከ2012 እስከ 2016 ባሉት የበጀት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአማካይ በየዓመቱ የ6 ነጥብ 8 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ እንደነበር በማስታወስ፤ በ2017 በጀት ዓመት የ9 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት የመካከለኛው ምሥራቅ የተፈጠረውን ዓለም አቀፍ ጫና ጭምር በመቋቋም የ10 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ታስመዘግባለች ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ በዓለም ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት ተርታ የሚያሰልፋትን ስኬት ማስመዝገቧን ገልጸው፤ ይህም የተቀናጀ የገንዘብና ፊሲካል ፖሊሲው ውጤት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡   ይሄውም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በጠንካራ መሠረት ላይ የተገነባ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ የሸቀጦችን የዋጋ ግሽበት ወደ ነጠላ አሃዝ ማውረድ አስችሏል ብለዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት የኢኮኖሚ አፈጻጸሙ በጥሩ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኝ በማንሳት፤ ስኬቱ የተረጋጋና የበለጸገ ኢኮኖሚ ለመገንባት የተጀመረውን ጥረት እንደሚያጠናክር ገልጸዋል፡፡ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትም በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በሁሉም የኢኮኖሚ አመላካቾች የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡ በ2019 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 10 ነጥብ 1 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብ እንደሚጠበቅና የቀረበው ረቂቅ በጀትም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተሳካ ሁኔታ ገቢራዊ ለማድረግና የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የሚፈጥረውን የኢኮኖሚ ጫና ጨምሮ የውጭ ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን ለመቋቋም ያለመ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የፌደራል መንግስትን ጠቅላላ ገቢ 1 ነጥብ 817 ትሪሊየን ብር ለማድረስ ታሳቢ መደረጉን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 6 ትሪሊየን ብር የሚሆነው ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱን አመላክተዋል። ለ2019 በጀት ዓመት የቀረበው አጠቃላይ 2 ነጥብ 339 ትሪሊየን ብር በጀት ከዘንድሮው በጀት ዓመት አንጻር የ21 ነጥብ 3 በመቶ እድገት እንዳለው ገልጸዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በተለያዩ ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቧን ገልጸዋል፡፡ ሪፎርሙ የውጭ ምንዛሪ በገበያ እንዲወሰን በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ክምችትን ማሳደግ፣ የዋጋ ግሽበትን ወደ ነጠላ አሃዝ መውረድና የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰትን ማሳደግ አስችሏል ብለዋል፡፡ ለ2019 በጀት ዓመት የቀረበው ረቂቅ በጀት ከባለፈው ዓመት የላቀ መሆኑ የመንግሥትን ግዙፍ የልማት ዕቅዶች ለማሳካት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡
በክልሉ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከተሞች ገጽታቸው እየተቀየረ ነው
Jun 11, 2026 185
ዲላ ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተሞችን በህብረተሰብ ተሳትፎ ገጽታቸውን በመቀየር ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ምቹ ማድረግ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ገለጹ። በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ 100 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነቡ የመሠረተ ልማቶች ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በወቅቱ እንዳሉት፤ በክልሉ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጋር በመቀናጀት በሚያከናውናቸው ተግባራት የከተሞች የተጎሳቆለ ገጽታ እየተቀየረ ነው ብለዋል።   ዛሬ በይርጋጨፌ ከተማ ለአገልግሎት የበቁ መሠረተ ልማቶች የዚሁ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በከተማው በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት የተጀመሩ መሠረተ ልማቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉና የውስጥ አቅምን አስተባብሮ ብልጽግናን የማረጋገጥ ሥራ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። በከተማው ሰው ተኮር የሆኑ ልማት ስራዎች ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን ጠቁመው በመኖሪያ ቤት አቅርቦት በኩል እየተከናወነ ያለው ስራም ተጠቃሽ መሆኑን አመልክተዋል ። በዞኑ ከተሞችን ውብና ጽዱ እንዲሁም ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ምቹ ከማድረግ አንጻር ውጤታማ ተግባር መከናወኑን ያነሱት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው።   በዞኑ በሚገኙ ከተሞች የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የጋራ መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ ይገኛል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ከተሞችን ፅዱና ለነዋሪዎች ምቹ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። የይርጋጨፌ ከተማ ከንቲባ አቶ ብዙአየሁ ታደሰ በበኩላቸው ፤ በህብረተሰብ ተሳትፎ ለአገልግሎት የበቁት የመሠረተ ልማት ተቋማት ለህብረተሰቡ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ናቸው ብለዋል።   ዛሬ ለአገልግሎት የበቁ መሰረተልማቶች የሌማት ትሩፋት ምርቶች መሸጫ ሼዶች፣ ድልድይ፣ መማርያ ክፍሎች እንዲሁም 40 መኖርያ ቤቶችን ያካተተ መሆኑን ጠቁመው ለመሰረተ ልማቶቹ ግንባታ 100 ሚሊዮን ብር ወጪ መደረጉን አንስተዋል። በከተማዋ መሶብ አንድ ማዕከልና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራ እየተፋጠነ እንደሚገኝና በቀጣይ ወር ለአገልግሎት እንደሚበቁ ተናግረዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ፍትሀዊ አገልግሎት መስጠት ያስችላል
Jun 11, 2026 224
ነቀምቴ፤ ሰኔ 4/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት አሰራርን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ፍትሀዊ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችል በኦሮሚያ ክልል የነቀምቴ ከተማዋ ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ ገለጹ። የነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።   በመርሃ ግብሩ የከተማዋ ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ እንደገለጹት፣ ማዕከሉ የመንግስት ተቋማት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ነው። የአገልግሎቱ ዲጂታላይዝድ መሆን ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ከመፍታት ባለፈ የተገልጋዩን ጊዜና ጉልበት እንደሚቆጥብም ተናግረዋል። የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ማስተናገድ የሚችለው ማዕከል ወደ ሥራ መግባት ማህበረሰቡ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ሲያነሳ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ይፈታል ብለዋል።   ማዕከሉ የተቋማትን አሰራር በማዘመን በ12 መስኮት 128 አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ መስጠት እንደሚያስችልም ገልጸዋል። ለማዕከሉ ግንባታ ከ400 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸው፣ ከ200 ሺህ በላይ የከተማዋን ነዋሪዎች እንደሚያገለግል ጠቁመዋል። በከተማዋ የተገነባው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቋማትን አሰራር በማዘመን ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት የራሱ ድርሻ እንዳለው በማዕከሉ አገልግሎት የሚሰጡ ባለሙያዎች ተናግረዋል።   ከአስተያየት ሰጪዎቹ ባለሙያዎች መካከል ተሰማ ሙለታ እንዳሉት መንግስት በአገልግሎት አሰጣጥ ህብረተሰቡ ሲያነሳው የነበረውን ቅሬታ ለመፍታት የዘረጋቸው አሰራሮች የሚበረታቱ ናቸው። ዘመናዊ አሰራሩ ከዚህ በፊት በፋይል መጥፋትና በአሰራር ችግር ይከሰት የነበረን የደንበኛ ምልልስ በመቅረፍ የተገልጋይ እርካታን እንደሚያሳድግ ገልጸዋል። ማዕከሉ ለሥራ ያለውን አመቺነት በመጠቀም የተገልጋይ እርካታን ለማሳደግ በትጋት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።   ሌላኛዋ የማዕከሉ ባለሙያ ወይዘሮ ለሊሴ ለታ ማዕከሉ ወደ ሥራ መግባቱ በመንግሥት መስሪያ ቤቶች ውስጥ የሚስተዋለውን የተገልጋይ እንግልት ለማስቀረት ይረዳል ብለዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ መንግስታዊ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ በማቀናጀት ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ፍትሃዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያግዝ ነው።
የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ስማርት አዲስ አበባን በመፍጠር እመርታዊ ውጤት እያስገኘ ነው
Jun 11, 2026 258
አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ስማርት አዲስ አበባን በመገንባት እመርታዊ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ገለጸ። በአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስተባባሪነት ችግር ፈቺ አሰራሮችን በነፃ በማልማት የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት እንዲጠቀሙ ያደረጉ የግል ተቋማትና ባለሙያዎች የእውቅና መርሃ ግብር ተካሂዷል።   የአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አዋሌ መሀመድ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን ላበለፀጉ ለአምስት ተቋማትና ዘጠኝ ባለሙያዎች እውቅና ተሰጥቷል። ስማርት ሲቲ አዲስ አበባን በመገንባት ሂደት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሙያዊ ዕውቀትና ክህሎታቸውን ለበጎ ዓላማ በማዋል ድጋፍ ላደረጉ የግል ተቋማትና ሙያተኞች ምስጋና አቅርበዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂም በስማርት ሲቲ ትግበራ አዲስ አበባን በመገንባት እመርታዊ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የአዲስ አበባ ተቋማት ለተገልጋዮች ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል አገልግሎት በመስጠት ዕድገትን የሚያሳልጥ ፈጣን የለውጥ ምኅዳር መፍጠራቸውን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ቱሉ ጥላሁን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የስማርት ሲቲ እሳቤና ግንባታ ከተማዋን ለነዋሪዎችና ጎብኚዎች ምቹ እያደረጉ ነው ብለዋል።   የስማርት ሲቲ ትግበራ ትብብርን የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው፤ ዛሬ እውቅና ያገኙ አካላትም የተቋማትን ችግር በመፍታት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መመለስ የሚያስችል ተግባር ማከናወናቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም አዲስ አበባ ያላትን ፀጋ ተጠቅማ ወደ ተሻለ ደረጃ እንድትሻገር የቴክኖሎጂ ሽግግርና ሌሎች የለውጥ ስራዎች ላይ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ዕውቅና ካገኙት መካከል የሜድኮ ቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ ከፍተኛ ፕሮጀክት አስተዳደር አቤል ደረጄ እንዳለው፤ የከነማ ፋርማሲ አሰራርን የሚያዘምንና የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ሲስተም አበልፅጓል።   ከጓደኛው ጋር በመሆን የመስሪያ ቦታ አሰጣጥ ስርዓቱን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል የሚቀይር ዘመናዊ የፈጠራ ሥራ አበርክተናል ያለው ደግሞ ጌታቢል መንግስቱ ነው።   ሁሉም ህብረተሰብ ባለው አቅም ሀገሩን ለማሳደግ የበኩሉን ሚና እንዲወጣም ወጣቶቹ ጥሪ አቅርበዋል።
በክልሉ ዘመናዊ የመንግስት አገልግሎትን ተደራሽ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል-ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
Jun 11, 2026 214
ዲላ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዘመናዊ የመንግስት አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ የማድረግ ውጤታማ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። የዲላ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬ በርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ጥላሁን ከበደ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።   ማዕከሉ በክልሉ ሦስተኛው ሲሆን ብዝሃ አገልግሎቶችን በማቀፍ ለማህበረሰቡ ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ተመላክቷል። ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በዚህ ወቅቱ እንዳሉት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰራርን ከማዘመን ባለፈ የአገልጋይነት ባህል የሚገነባና የተገልጋይ እርካታን የሚያሻሽል ነው። በተለይ ብዝሀነት ባለበት እንደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዜጎችን እንግልት በመቀነስ ረገድ ድርሻው የጎላ ነው ብለዋል። በክልሉ ዘመናዊ የመንግስት አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ የማድረግ ውጤታማ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል። የለውጡ መንግስት ዘመናዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ ከአንድ ማዕከል አገልግሎት እስከ ሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም የደረሰ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወኑን ያነሱት ደግሞ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) ናቸው።   በማዕከሉ በአራት የፌደራል እና በአምስት የክልል ተቋማት የሚሰጡ 32 የተለያዩ የአገልግሎት አይነቶች ይሰጣሉ ብለዋል። ይህም በአንድ ማዕከል የዜጎችን ክብር በጠበቀ መልኩ ብዙ አገልግሎቶችን ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረው፣ መሰል አገልግሎቶችን የማስፋት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የዲላ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በወላይታ ሶዶ እና በአርባ ምንጭ ከተሞች ከተገነቡት ቀጥሎ ሦስተኛው መሆኑ ታውቋል።
የነዋሪዎችን መረጃ በዘመናዊ መንገድ የማደራጀት ሥራ ለአገልግሎት አሰጣጥ መሳለጥና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ ሚና አለው
Jun 11, 2026 326
አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት መረጃዎችን በዘመናዊ መንገድ ለማደራጀት እየተከናወነ ያለው ሥራ የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ከማድረግ ባለፈ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለፁ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎችን መረጃ በዘመናዊ መንገድ ለማደራጀት እየተከናወነ ያለውን ተግባር ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ እንደሀገር የዲጂታላይዜሽን ሥራ በተግባር የሚታይበት ደረጃ ደርሷል። በተለይም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የተሰሩ ስኬታማ ሥራዎች አይተኬ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም እነዚህ ስኬታማ ሥራዎች ይበልጥ ለማጠናከር መረጃን የሚያሰባስቡ ማናቸውም የሕዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አሰራራቸውን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ማሻገር አለባቸው ብለዋል። በተለይም በሲቪል ምዝገባ ረገድ ከውልደት እስከ ሞት ያሉ ማንኛቸውም የነዋሪዎችን መረጃዎችና ሰነዶች ከባህላዊ የወረቀት አያያዝ ወጥተው በዲጂታል መንገድ መያዝ እንዳለባቸው ተናግረዋል። ይህም ተቋማዊ አሰራርን በማዘመን ረገድ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ የመረጃዎች ዲጂታል መሆን ቢሮክራሲን በማስቀረት ፍጹም ግልፀኝነትን ያረጋገጠ አሰራር ለመዘርጋት እንደሚያስችል ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የያዘችውን የዲጂታል 2030 ራዕይ ስኬታማ ለማድረግ የበኩሉን ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት አመላክተዋል። በዚህ ረገድ የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የጀመረው የሰነድ አስተዳደር ሥርዓት በሁሉም የመንግሥት ተቋማት ዘንድ ተሞክሮው ሊሰፋ የሚገባው ነው ብለዋል። ይህም ዜጎች በቀላሉ መረጃዎችን ማግኘት የሚችሉበትን የኦንላይን አገልግሎት ሥርዓት ለመዘርጋት እንደ ማሳያ የሚወሰድ ተግባር መሆኑም አስረድተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በበኩላቸው፤ ህዝቡ በቤቱ ሆኖ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለውን አዲስ የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት ሰፊ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል።   ይህም ለዘመናዊ አገልግሎት አሰጣጥ መሰረት እንደሆነ ተናግረው፤ተገልጋዩ አገልግሎቱን በኦንላይን ይጠይቃል፣ እኛም በቀጥታ የምንሰጥበትን ቀልጣፋ ሂደት ይፈጥራል ብለዋል። አሰራሩ ተግባራዊ መደረጉ የአገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን እንግልትን ሙሉ በሙሉ እንደሚያስቀር ተናግረዋል።
ስፖርት
ዋና ጠቅላይ መምሪያው ከተሰጠው ተልዕኮ በተጨማሪ የሀገርን ክብር በአደባባይ ከፍ የሚያደርጉ ስፖርተኞችን እያፈራ ይገኛል
Jun 11, 2026 263
አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከተጣለበት ሰላምን የማስጠበቅ ተልዕኮ በተጨማሪ የሀገርን ክብር በዓለም መድረክ ከፍ የሚያደርጉ ስፖርተኞችን እያፈራ እንደሚገኝ የመምሪያው አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ ገለጹ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በ2018 ዓ.ም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የፖሊስ አባል ስፖርተኞች የማዕረግ እድገት፣ የገንዘብ ሽልማት እንዲሁም የእውቅናና ምስጋና መርሃ-ግብር አካሂዷል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ፍጹም ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፖሊስ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ለዚህም ለመዲናዋ የፖሊስ አባላት በሙሉ የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከተጣለበት ሰላምን የማስጠበቅ ተልዕኮ በተጨማሪ የሀገርን ክብር በዓለም አቀፍ የስፖርት አደባባይ ከፍ የሚያደርጉ ስፖርተኞችን እያፈራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከተቋሙ የሚወጡ ስፖርተኞች በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ውድድሮች ድልን በመቀዳጀት በርካታ ሜዳሊያዎችን በማስመዝገብ የሀገሪቷ ክብር በዓለም አደባባይ ጎልቶ እንዲታይ አድርገዋል ብለዋል። ይህ አበረታች ውጤት ሊገኝ የቻለው ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ እንደሆነም ተናግረዋል። የተካሄደው የእውቅና መርሃ ግብር ባለድል ስፖርተኞችን ለማበረታታት ያለመ ሲሆን፤ በቀጣይም የፖሊስ ተቋማት የተተኪ ስፖርተኞች ምንጭ ሆነው እንዲቀጥሉ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዩጋንዳ ጋር አቻ ተለያየ
Jun 11, 2026 158
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዩጋንዳ አቻው ጋር ዛሬ ባደረገው ጨዋታ ሶስት አቻ ተለያይቷል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሊዲያ ኢያሱ ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር ምኅረት አየለ ቀሪዋን ጎል ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ናማኩላ ጆን፣ ባቢሬ ማርታ እና ያጋላ ፍላቪያ ለዩጋንዳ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጨዋታው አዝናኝ እና ተመጣጣኝ ፉክክር ተደርጎበታል። የወዳጅነት መርሐ ግብሩ ኢትዮጵያ ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ከዛምቢያ ጋር የምታደርገው ወሳኝ የመጨረሻ ዙር የማጣሪያ ጨዋታ ዝግጅት አካል መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። አሰልጣኝ ራውዳ ዓሊ ከዛምቢያ ጋር ለሚደረገው ዝግጅት ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ ማድረጋቸው ይታወቃል። ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ከትናንት በስቲያ በካፍ የልህቀት ማዕከል ዝግጅት ማድረግ ጀምረዋል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዛምቢያ ጋር የመጨረሻ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ሰኔ 27 እና ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ያከናውናል። ኢትዮጵያ በድምር ውጤት ካሸነፈች በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ታልፋለች። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል።
ዓለም ዋንጫን የሚያስተናግዱት 16 ስታዲየሞች 
Jun 11, 2026 462
በሙሴ መለሰ 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ ጣምራ አዘጋጅነት ዛሬ በይፋ ይጀምራል። ይህ ውድድር በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የ32 ሀገራትን ቁጥር በማሳደግ 48 ሀገራት ተሳታፊ የሚሆኑበት ታላቅ መድረክ ነው። ውድድሩ በሶስቱ ሰሜን አሜሪካ ሀገራት በሚገኙ 16 ከተሞች ውስጥ በተመረጡ 16 ስታዲየሞች የሚካሄድ ሲሆን፣ በእያንዳንዱ ከተማ ውስጥ ውድድሩን የሚያስተናግድ አንድ አንድ ስታዲየም ብቻ ተዘጋጅቷል። ጨዋታዎቹን በደመቀ ሁኔታ ለማስተናገድ የተመረጡት ስታዲየሞችም፦ በአሜሪካ የሚገኙ ስታዲየሞች 1. ሜትላይፍ ስታዲየም (ኒው ዮርክ/ኒው ጀርሲ) እ.አ.አ በ2010 ስራ የጀመረው ይህ ስታዲየም 82,500 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም አለው። ስታዲየሙ እጅግ በጉጉት የሚጠበቀውን የፍጻሜ ጨዋታ ጨምሮ በአጠቃላይ 8 ጨዋታዎችን ይካሄድበታል። 2. ኤቲ ኤንድ ቲ ስታዲየም (ዳላስ፣ ቴክሳስ) እ.አ.አ በ2009 አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ ስታዲየም 94,300 ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፣ ከውድድሩ ስታዲየሞች ሁሉ በትልቅነቱ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል። በአጠቃላይ 9 ጨዋታዎችን በማስተናገድ ከሁሉም ስታዲየሞች በርካታ ጨዋታዎች የሚደረጉበት ስታዲየም ነው። 3. ሶፊ ስታዲየም (ሎስ አንጀለስ፣ ካሊፎርኒያ) እ.አ.አ በ2020 የተገነባውና ዘመናዊው ሶፊ ስታዲየም 70 ሺህ 240 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም አለው። የአዘጋጇ አሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ከፓራጓይ ጋር የሚያደርገውን የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ጨምሮ ስምንት ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። 4. ሜርሴዲስ ቤንዝ ስታዲየም (አትላንታ፣ ጆርጂያ) እ.አ.አ በ2017 ስራ የጀመረው ይህ ስታዲየም 71 ሺህ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም አለው። ስታዲየሙ ለአለም ዋንጫው ማጠናቀቂያ ወሳኝ ከሆኑት ጨዋታዎች አንዱ የሆነውን የአንዱን ግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ጨምሮ በአጠቃላይ 8 ጨዋታዎችን እንዲያስተናግድ ተመርጧል። 5. ሃርድ ሮክ ስታዲየም (ሚያሚ፣ ፍሎሪዳ) እ.አ.አ በ1987 የተገነባውና ረጅም አገልግሎት የሰጠው ሃርድ ሮክ ስታዲየም 64,767 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም አለው። ይህ ስታዲየም የደረጃ ጨዋታን ጨምሮ 7 ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። 6. አሮው ሄድ ስታዲየም (ካንሳስ ሲቲ፣ ሚዙሪ) እ.አ.አ በ1972 ስራ የጀመረውና አንጋፋው አሮው ሄድ ስታዲየም 76 ሺህ 416 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን፣ በውድድሩ ወቅት 6 ጨዋታዎችን በስታዲየሙ ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል። 7. ኤንአርጂ ስታዲየም (ሂውስተን፣ ቴክሳስ)፦ እ.አ.አ በ2002 ስራ የጀመረው ኤንአርጂ ስታዲየም 72 ሺህ 220 ተመልካቾችን የመያዝ ከፍተኛ አቅም ያለው ሲሆን፣ በአጠቃላይ 7 የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። 8. ጂሌት ስታዲየም (ቦስተን፣ ማሳቹሴትስ) እ.አ.አ በ2002 ዓ.ም ስራ የጀመረውና በስፖርቱ አለም ታዋቂ የሆነው ጂሌት ስታዲየም 65,878 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን፣ 7 ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ተመርጧል። 9. ሊንከን ፋይናንሻል ፊልድ ስታዲየም (ፊላዴልፊያ፣ ፔንስልቬንያ) እ.አ.አ በ2003 ስራ የጀመረው ይህ ስታዲየም 67,594 ተመልካቾችን በስታዲየሙ ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፣ 6 ጨዋታዎችን እንደሚያስተናግድ ታውቋል። 10. ሉመን ፊልድ ስታዲየም (ሲያትል፣ ዋሽንግተን) እ.አ.አ በ2002 ስራ የጀመረው ሉመን ፊልድ ስታዲየም 69 ሺህ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም አለው። ስታዲየሙ በውድድሩ ወቅት 6 ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። 11. ሌቪስ ስታዲየም (ሳን ፍራንሲስኮ፣ ካሊፎርኒያ) እ.አ.አ በ2014 ወደ አገልግሎት የገባው ሌቪስ ስታዲየም 68,500 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን፣ በአጠቃላይ 6 ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ዝግጁ ሆኗል። በሜክሲኮ የሚገኙ ስታዲየሞች 12. አዜቴካ ስታዲየም (ሜክሲኮ ሲቲ)፦ እ.አ.አ በ1966 ዓ.ም ስራ የጀመረውና ታሪካዊ ስታዲየም አዜቴካ ስታዲየም፣ ለዚህ ዓለም ዋንጫ ከፍተኛ እድሳት ተደርጎለታል። በአሁኑ ወቅት 87 ሺህ 523 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን፣ መላው ዓለም በጉጉት የሚጠብቀውን የዓለም ዋንጫውን የመክፈቻ ጨዋታ ጨምሮ 5 ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። አዜቴካ ስታዲየም (Estadio Azteca) የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ በማስተናገድ በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ሶስት የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታዎችን ያስተናገደ ብቸኛው ስታዲየም የመሆን አዲስ ታሪክ ይሰራል። 13. ቢቢቪኤ ስታዲየም (ሞንቴሬይ) እ.አ.አ በ2015 የተመረቀው ዘመናዊው ቢቢቪኤ ስታዲየም 53,500 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን፣ በአጠቃላይ 4 ጨዋታዎች ይደረጉበታል። 14. አክሮን ስታዲየም (ጓድላሀራ) እ.አ.አ በ2010 ዓ.ም ስራ የጀመረው አክሮን ስታዲየም 48,071 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን፣ በውድድሩ ወቅት 4 ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። በካናዳ የሚገኙ ስታዲየሞች 15. ቢሲ ፕሌስ ስታዲየም (ቫንኩቨር) እ.አ.አ በ1983 ስራ የጀመረውና እ.አ.አ በ2011 ዘመናዊ እድሳት የተደረገለት ቢሲ ፕሌስ ስታዲየም 54,500 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም አለው። ይህ ስታዲየም 7 ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። 16. ቶሮንቶ ስታዲየም (ቶሮንቶ) እ.አ.አ በ2007 ስራ የጀመረው ይህ ስታዲየም ለዓለም ዋንጫው ዝግጅት ሲባል የመቀመጫ ቁጥሩ እንዲጨምር ተደርጓል። ስታዲየሙ 45,000 ተመልካቾችን የሚይዝ ሲሆን ይህም ከሁሉም የውድድሩ ስታዲየሞች በመያዝ አቅሙ ትንሹ ያደርገዋል። የካናዳ ብሔራዊ ቡድን የሚያደርገውን የመጀመሪያ ጨዋታ ጨምሮ 6 ጨዋታዎችን ያስተናግዳል። ከአጠቃላይ 104 ጨዋታዎች ውስጥ አሜሪካ 78 ጨዋታዎችን፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ በተመሳሰይ 13 ጨዋታዎችን ያስተናግዳሉ። ለዓለም ዋንጫው ዝግጅት ብቻ በ16ቱም ስታዲየሞች ላይ ለተደረጉ ማሻሻያዎች (ሜዳዎችን ከተፈጥሮ ሳር ጋር ማላመድ፣ የክብር እንግዶች መቀመጫዎችን ማደስ እና የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን መዘርጋትን ጨምሮ) በአጠቃላይ ከ1 ቢሊዮን እስከ 1.5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚጠጋ ወጪ እንደወጣ ይገመታል። ይህ ቁጥር ከቀደሙት ዓለም ዋንጫዎች (ለምሳሌ በኳታር ስተናጋጅነት በተካሄደው 22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ 200 ቢሊዮን ዶላር) አንጻር በጣም ያነሰ ሲሆን ይህም የሆነበት ምክንያት አዳዲስ ስታዲየሞች ባለመገንባታቸው እና ሁሉም ስታዲየሞች አስቀድመው ዝግጁ የነበሩ በመሆናቸው ነው።  
አካባቢ ጥበቃ
ኮሌጁ የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው የተሻሻሉ ችግኞችን በማዘጋጀት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው
Jun 11, 2026 307
ሚዛን አማን፣ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፡-የሚዛን ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚሆኑና የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው የተሻሻሉ ችግኞችን በማዘጋጀት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ገለጸ። ኮሌጁ የማኅበረሰብ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችን ለማስፋፋት በጥናትና ምርምር የታገዘ ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አስታውቋል።   የኮሌጁ ምክትል ኃላፊ አቶ ጥላሁን አለማየሁ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኮሌጁ በአረንጓዴ ልማት ሥራ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ችግኞችን በማዘጋጀት ለማኅበረሰቡ እያሰራጨ ነው። በተለይ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን ውጤታማነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለዘንድሮ ተከላ ከ250 ሺህ በላይ በምርምር የተደገፉና የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን አዘጋጅቷል ብለዋል። ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል ከዛፍ ጋር ትስስር ያላቸው ቁንዶ በርበሬ እና ቡናን ጨምሮ የሻይ ቅመም፣ የፍራፍሬ፣ የውበትና የጥላ ዛፎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። የችግኝ ዝርያዎቹ ፈጥነው እንዲደርሱ፣ በሽታ እንዲቋቋሙና ምርታማነታቸው የተሻለ እንዲሆን ኮሌጁ ከተለያዩ የግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱንም አቶ ጥላሁን አክለዋል። የተዘጋጀውን ችግኝ ለማህበረሰቡ ከማሰራጨት ባሻገር ኮሌጁ በራሱ እንደሚተክል ገልጸው በዚህም የውስጥ ገቢውን ከማሳደግ ባለፈ ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር በምግብ ራስን ለመቻልና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አመልክተዋል።   በኮሌጁ ችግኝ ጣቢያ የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸው እየሰሩ ካሉ ወጣቶች መካከል መሠረት ታፈሰ በችግኝ ጣቢያው በዘርፉ ባለሙያዎች ታግዛ በመሥራት የቀሰመችው ሙያ በራሷ ችግኝ የማዘጋጀት አቅምን ለማጎልበት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላት ገልጻለች። የተዘጋጁ ችግኞችን የመከታተልና የመንከባከብ ሥራ በመሥራት ቤተሰባቸውን እያስተዳደሩ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ እልፍነሽ ተገኝ እና ታጋይነሽ ዘውዴ ናቸው።   የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ከተጀመረ ወዲህ ኮሌጁ ችግኞችን በብዛት እያዘጋጀ በመሆኑ ዓመቱን ሙሉ የሥራ ዕድል በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸወን ተናግረዋል።    
በክልሉ ከብክለት የፀዳ ከባቢን በመፍጠር ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራት እየተደረገ ያለው ጥረት ይጠናከራል
Jun 10, 2026 595
ሆሳዕና ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ) ፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከብክለት የፀዳ ከባቢን በመፍጠር ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራት እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ገለፀ። ቢሮው "ብክለትን እንቀንስ፣ እንከላከል" በሚል መሪ ሐሳብ ከአምራች ኢንዱስትሪዎች፣ ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በህግ ተከባሪነት ዙሪያ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል።   የቢሮው ኃላፊ አቶ አብርሃም መጫ በወቅቱ እንዳሉት፤ በክልሉ ከብክለት የፀዳ ከባቢን በመፍጠር ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራት እየተደረገ ያለው ጥረት ይጠናከራል። ለዚህም ከኢንዱስትሪዎች የሚወገዱ ቆሻሻዎችን በአግባቡ የማስወገድ ስራ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ጠቁመው ይህንንም ለማጠናከር የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። በክልሉ የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚን ለመንገባት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የፅዱ ኢትዮጵያ ኢንሼቲቮች ትግበራ መከናወኑን ጠቅሰዋል። በተለይም ከብክለት የጸዳ አካባቢን ለመፍጠር በተደረጉ ጥረቶች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶችን ለማስፋት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባም አሳስበዋል።   ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል በሆሳዕና ከተማ የምስጋና ዱቄት ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ደመቀ በበኩላቸው ፋብሪካው ተረፈ ምርቶችን በአግባቡ በማስወገድ አካባቢውን ከብክለት ለመጠበቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለስኬቱም የተረፈ ምርት ማስወገጃን የማዘጋጀትና ምድረ ግቢውን በአረንጓዴ ልማት የመሸፈን ተግባር መከናወኑን አስረድተዋል። ፋብሪካው በጤና ባለሙያዎች ድጋፍና ክትትል ከብክለት የፀዳ አካባቢን ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በወራቤ ከተማ የአበሩስ ዱቄት ፋብሪካ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ነስሬ ናቸው።   ፋብሪካው ለፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ሴፍቲ ታንክን በመጠቀም ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት መስጠቱን ጠቁመዋል። በቀጣይም ፋብሪካው ንፅህናው የተጠበቀ ምርትን ለማህበረሰቡ ተደራሽ የማድረግ ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የክልል ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሀገር በቀል የአካባቢ ጥበቃ ባህልን በማጠናከር ተፈጥሮን የመንከባከብ ሥራ እየተከናወነ ነው
Jun 10, 2026 460
ዲላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሀገር በቀል የአካባቢ ጥበቃ ባህልን በማጠናከር ተፈጥሮን የመንከባከብ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ የአካባቢ ጥበቃና የአየር ለውጥ ባለስልጣን ገለጸ። በክልሉ ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ቀን "ለአየር ንብረት ለውጥ ተግባራዊ እርምጃ" በሚል መሪ ሀሳብ በአከባቢ ጽዳት፣ በችግኝ ተከላ እና በፓናል ውይይት በዲላ ከተማ ተከብሯል። ቀኑ ስለአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ ከመፍጠር ባለፈ ተግባራዊ እርምጃ ማጠናከርን ዓላማ ያደረገ መሆኑ ተመላክቷል። የ‎ባለስልጣኑ ሃላፊ ግዛቴ ግጄ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ የሚያስከትለውን አደጋ ለመቀነስ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ጥረት እየተደረገ ነው። በተለይ በጌዴኦ፣ ኮንሶ፣ የኦሞ ሸለቆዎችና መሰል የክልሉ አካባቢዎች በሀገር በቀል የአካባቢ ጥበቃ ባህል ዓለም አቀፍ እውቅና እንዳላቸው አንስተው ይህንን በማጠናከር ተፈጥሮን የመንከባከብ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም በአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ አልፎም የታዳሽ ሃይል አጠቃቀምን በማሻሻል ብክለትን በመቀነሱ በኩል ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። ‎የአካባቢ ጥበቃ የጋራና የተቀናጀ ተግባራዊ ምላሽ ይፈልጋል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው። ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ተከላ በማከናወን ዞኑ የሚታወቅበትን ሀገር በቀል የአካባቢ ጥበቃ እውቀት ከማጠናከር ባለፈ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል። ‎የዲላ ከተማ ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው ከአየር ንብረት ተጽዕኖ ነጻ የሆነች ከተማ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። በከተማው የተከናወኑ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት እንዲሁም የችግኝ ተከላና የጽዳት ስራዎች ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ መቀነስ የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል
Jun 8, 2026 1247
ባህር ዳር፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን የክልሉ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። ዓለም አካባቢ ቀን "የአየር ንብረት ለውጥ ተጽኖን መታደግ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል።   የባለስልጣኑ ዋና ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ በመድረኩ እንደገለጹት፣ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያገዘ ነው። የኮሪደር ልማትም ከተሞችን ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ በማድረግ የአካባቢ ጥበቃንና እንክብካቤ ሥራ እንዲፋጠን አስተዋጾ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ማንኛውም የልማት ፕሮጀክት ዘላቂነቱ የሚረጋገጠው ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በተጣጣመ መልኩ ሲተገበር መሆኑን ገልጸው፣ ይህም በክልሉ ተግባራዊ መደረጉን ጠቁመዋል። በክልሉ የልማት ሥራዎች ከአየር ንብረት ጋር ተጣጥመው እንዲከናወኑ መደረጉ እንደ ጎርፍ እና በረሀማነት ያሉ ችግሮችን ለመቀነስ መቻሉን ተናግረዋል። በአማራጭ የሃይል አቅርቦት ላይ የተመሰረተ ልማትም የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን አስረድተዋል። የአካባቢ ብክለትን ለመከላከልም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለህብረተሰቡ በዘመናዊ ቆሻሻ አወጋገድ ላይ ትምህርት በመስጠት ለውጥ እየታየ መምጣቱን ጠቁመዋል። ይህም ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በባለስልጣኑ የአየር ንብረት ለውጥ አካቶ ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አወቀ ይታይ የመወያያ ጽሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በግብርና፣ በትራንስፖርትና በከተማ ልማት ዘርፎች የአየር ንብረት ጉዳይን አካቶ እየተሰራ ነው።   በማሳያነትም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና በኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 6723
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 5980
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 4810
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 4715
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 6516
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 5431
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው።   መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው።   በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል።   ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር።‎ ‎በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።   የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል።   በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል።   የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።   በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው።   በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል።   ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡   የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል።   በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል።   የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ።   በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል።   ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።   ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል።   በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ።   በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል።   የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል።   የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።  
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 5018
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 5247
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል።   በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል።   በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል።   የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።      
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Jun 7, 2026 2368
ባሳለፍነው ሳምንት … ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባሳለፍነው ሳምንት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተካሂዷል። ድምፅ ለመስጠት 54 ሚሊየን 57 ሺህ 861 መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማሳወቁ ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለመራጮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምርጫው ወቅት ድምጽ ስለሰጡ መራጮች ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ማገልገል መታደል መሆኑን ገልጸው፤ ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይህንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ ሲሉም አስገንዝበዋል። ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ሥራ አስጀምረዋል። ‎ ‎በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ ‎በአጠቃላይ 22 ነጥብ 25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን ይሸፍናል። ይህ ፕሮጀክት የማይቆራረጥ የልማት ሥራችን ኅያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሀገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና 73 አባላት ከያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል። ‎ ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ከአኅጉራችን ነባራዊ ሁኔታና ተሞክሮ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ አፍሪካዊ ተቋማት ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የምርጫ ሂደታችንን ለመደገፍ በመላው ሀገሪቱ ታዛቢዎችን በማሰማራት የምርጫ ታዛቢ ልዑኩ ላደረገው ያልተቆጠበ ጥረት እውቅና እና አድናቆት እየሰጠን፤ የምልከታውን የተሟላ ውጤት እንጠብቃለን ሲሉም አመላክተዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻ ልማት፤ የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳን የያዘ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ‎ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽንም፤ ከወንዞቹ ባሻገር እስከ 50 ሜትር የሚዘልቅ መሆኑን አስረድተዋል። የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን እና የንግድ ቦታዎችን ልማት ማካተቱን ጠቅሰው፤ ከተማዋን በእጅጉ የቀየረ ነው ብለዋል። ‎ የወንዝ ዳርቻዎችን ገጽታ እና አገልግሎት ከማሻሻል ባለፈ በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስ እና በተያያዙ ዘርፎች ለብዙ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም አብራርተዋል። አብዛኛው ሥራ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች መቀረጹና መተግበሩ፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት እና በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው ዐቅም እያደገ መምጣቱን ያሳያል ነው ያሉት። ‎ ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎች እና ቆሻሻዎች የሚጣሉባቸው፣ በወንዝ ዳርቻዎች በሚኖሩ ማኅበረሰቦች ላይ የጎርፍ አደጋ ይጋርጡ የነበሩት እነዚህ አካባቢዎች፤ አሁን ላይ ወደ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ለሕይወት ምቹ ወደሆነ የከተማ ቦታነት እየተቀየሩ መሆኑንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ሁኔታም፤ የንግድ እና የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ከዚህ ቀደም ከነበረው ያልተናበበ ሥራ ተላቀው በጥናትና በጋራ ግብ ተባብሮ መሥራት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ስለመሆኑ አመላክተዋል። ‎ይህ ፈጣን የልማት ሥራ አዲስ አበባን አረንጓዴ፣ ይበልጥ የተሳሰረች፣ በኢኮኖሚ ንቁ እና ሰውን ማዕከል ያደረገች ከተማ የማድረግ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ላይ መሰረት የተጣለበት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ
በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ …
Jun 3, 2026 2856
በዮሐንስ ደርበው በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር ሞላወርቅ አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በዓለምም ሆነ በሀገራችን አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው የደም ግፊት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በቆይታቸውም፤ ለደም ግፊት አጋላጭ ስለሆኑ ምክንያቶችና ሊደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄም እንዲሁም ከመድሃኒት አወሳሰድ ጋር በተያያዘ ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አቅርበዋል። · የደም ግፊት ምንድን ነው? ደም በደም ሥሮቻችን ሲያልፍ፤ የሚለካው መጠን “የደም ግፊት” እንደሚባል ዶክተር ሞላወርቅ ያስረዳሉ። የላይኛው (ሲስቶሊክ ወይም ከፍተኛው) የደም ግፊት መጠን ልብ በምትኮማተርበት ጊዜ ደም ወደ ደም ሥር ሲረጭ የሚለካው መሆኑንም ይገልጻሉ። የታችኛው (ዲያስቶሊክ ወይም ዝቅተኛው) የደም ግፊት መጠን ደግሞ ልብ ደም ለመቀበል ለአፍታ ዕረፍት በምታገኝበት ጊዜ የሚከሰት የግፊት ደረጃ መሆኑንም ይገልጻሉ። · የደም ግፊት ደረጃዎች እና ማስጠንቀቂያቸው ዶክተር ሞላወርቅ እንደሚሉት፤ የጤናማ ሰው የደም የግፊት መጠን 120 በ 80 እና በታች መሆን ይኖርበታል። በሌላ በኩል ግን ይላሉ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 የታችኛው ደግሞ ከ80 በታች ከሆነ “ከፍ ያለ ወይም የጨመረ የደም ግፊት ደረጃ” ይባላል። የላይኛው ከ130 እስከ 139 ወይም የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከሆነ ደግሞ “ደረጃ አንድ የደም ግፊት” እንደሚባል ያስረዳሉ። የላይኛው ከ140 በላይ ሲሆን እና የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ ደግሞ “ደረጃ ሁለት የደም ግፊት” እንደሚባል ነው የሚገልጹት። በሌላ በኩል “የከፋ የደም ግፊት ደረጃ” የሚባል እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም የላይኛው ከ180 በላይ እና የታችኛው ከ120 በላይ ሲሆን ነው በማለት ያብራራሉ። · ለደም ግፊት መጨመር መንስዔዎቹ ምንድን ናቸው? በዋናነት ሁለት ዓይነት የደም ግፊት መኖሩን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ ከፍተኛ የደም ግፊት እና መንስዔው የሚታወቅ የደም ግፊት መሆኑን አስረድተዋል። በዋናነት ወይም በአብዛኛው ከ90 እስከ 95 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ደም ግፊት የሚባለው መሆኑን ገልጸው፤ በርካታ መንስዔዎች ሊኖሩት እንደሚችሉ ቢገመትም ሁሉም በውል እንደማይታወቁ ያነሳሉ። ከበርካታ መንስዔዎቹ መካከልም፤ በቤተሰብ የሚወረስ (ተላላፊ)፣ አካባቢያዊ ምክንያቶች እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ የሚሉት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። የአኗኗር ዘይቤ ሲባልም፤ የአመጋገብ ሥርዓት በተለይም ጨው የበዛበት ምግብ፣ ክብደት መጨመር፣ አካባቢያዊ ሁኔታዎች (አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ)፣ የስኳር ታማሚ መሆን የሚሉት ይጠቀሳሉ ይላሉ። · ለደም ግፊት በተለይም እነማን ተጋላጭ ናቸው? ዕድሜ በጨመረ ቁጥር የደም ግፊት የመከሰት ዕድሉም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በዚህም መሠረት ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ይናገራሉ። እንዲም በቤተሰብ የደም ግፊት ኬዝ ያለባቸው ሰዎች፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒክ ግሩፕ) ለምሳሌ፡- በጥቁሮች (አፍሪካውያን)፣ በኤስያውያን፣ በደቡብ ኤስያውያን ላይ ከፍተኛ የደም ግፊት ሊከሰት እንደሚችል ይገልጻሉ። እንደ ዶክተር ሞላወርቅ ማብራሪያ፤ በአጠቃላይ አጋላጭ ምክንያቶች በሁለት ተከፍለው ሊታዩ ይችላሉ። አንደኛው፡- ልንከላከላቸው (ልንቀንሳቸው) የምንችላቸው መሆናቸውን በመግለጽ ይህም የአመጋገብ ሥርዓትን ማስተካከል፣ ክብደት መቀነስ፣ አልኮልና ሲጋራ ማቆም እና መሰል መሆናቸውን አብራርተዋል። ሁለተኛው፡- ልንከላከላቸው የማንችላቸው መሆናቸውን ገልጸው ይህም፤ የዕድሜ መጨመር፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒሲቲ) እና በቤተሰብ የሚተላለፍ የሚሉትን ጠቅሰዋል። · የደም ግፊትን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? የደም ግፊ ከተከሰተ መቆጣጠር እንጅ ማዳን እንደማይቻል ገልጸው፤ ከላይ እንደተጠቀሰው አስቀድሞ መከላከል ወይም ማዘግየት የሚቻል እና መከላከል የማይቻል የደም ግፊት ደረጃ መኖሩን አስረድተዋል። · የደም ግፊት በውል የሚታወቅ ምልክት አለው? የደም ግፊት ሲከሰት ምልክት እንደሌለው በማንሳት፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ “ዝምተኛው ገዳይ” እስከመባል መድረሱን ዶክተር ሞላወርቅ ያነሳሉ። ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ግን፤ በአንድ ወይም በሁለት የሰውነት አካል ላይ ችግር ሊደርስ እንደሚችል ከዚህም ሲያልፍ እስከ ሞት እንደሚያደርስ ይጠቅሳሉ። በተያያዘም፤ የራስ ምታት፣ የዐይን ብዥ ብዥ ማለት፣ ትንፋሽ ማጠር፣ የድካም ስሜት፣ አንገት የመያዝ ዓይነት ስሜቶች የደም ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ሊስተዋሉ የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል። አክለውም፤ በአብዛኛው በሕብረተሰቡ ላይ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርስና ድንገት በጨመረ ጊዜ፤ ለሞት፣ ለአደጋ፣ ለልብ ድካም፣ አጣዳፊ ለሆነ የልብ ህመም፣ በጭንቅላት ላይ የደም መፍሰስ፣ የኩላሊት ድክመት፣ በደም ሥሮች በአግባቡ ደም እንዳይተላለፍ ማድረግ፣ ለዐይነ ስውርነት መዳረግን ጨምሮ መሰል ጉዳቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝበዋል። · መድኃኒት አወሳሰድ ላይ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ ዶክተር ሞላወርቅ እንደገለጹት፤ አንድ ሰው ደም ግፊት እንዳለበት ከተነገረው በኋላ ሕክምናውም እንደ ደም ግፊቱ ደረጃ ይለያያል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 ከሆነ “የጨመረ ግፊት” ይባላል፤ እዚህ ላይ ሰውየው ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አመጋገቡን እንዲያስተካክል፣ ስፖርት እንዲሠራ፣ ክብደት እንዲቀንስ፣ ሱስ (ሲጋራ፣ አልኮል) እንዲቀንስ ክትትል ይደረጋል ብለዋል። ስለዚህ መድኃኒት ሳይጀምር የአኗኗር ዘይቤን በማስተካከል የደም ግፊቱን ሊቀንሰው (ሊቆጣጠረው) ይችላል ማለት ነው ሲሉም ይገልጻሉ። “ደረጃ አንድ ግፊት” የሚለው ላይ ከደረሱ ግን ሕክምና የሚጀምሩም የማይጀምሩም እንዳሉ ተናግረዋል። ይህም ማለት የላይኛው ከ130 እስከ 139 የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከደረሰ ሕክምና የሚጀምሩት የስኳር ህመም ያለባቸው፣ የስትሮክ ህመም ያለባቸው፣ ከልብና ደም ሥር የተገናኙ ህመሞች ያሉባቸው ከሆኑ ቢያንስ አንድ የግፊት መድኃኒት መጀመርና ክትትል ማድረግ አለባቸው ይላሉ። በሌላ በኩል ግን ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ ሰዎች “ደረጃ ሁለት ግፊት” ላይ ከደረሱ (የላይኛው ከ140 የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ) ሁሉም መድኃኒት መጀመር እንዳለባቸው በአጽንዖት ገልጸዋል። የሚጀምሩት መድኃኒትም አሁን ባለው በተሻሻለው የሕክምና ዘይቤ ሁለት መድኃኒቶች የሚጀምሩበት ሁኔታ እንዳለ ነው የሚያስረዱት። የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ግን ለሁሉም የግፊት ዓይነቶች መሠረት (የሚመከር) መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ መድኃኒት ጀምሬያለሁ ብሎ የአኗኗር ዘይቤው ላይ ቸልተኝነት ሊኖር እንደማይገባም ነው የሚመከሩት። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከግፊት ጋር በተያያዘ ወደ ሆስፒታል መጥተው የሚታከሙ ታካሚዎች አብዛኞቹ፤ ጀምረው ያቋረጡ፣ ለመጀመር ፍላጎት የሌላቸው፣ ቅድመ ምርመራ ባለማድረግ ምክንያት ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ የተጎዱ ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። ስለዚህ የግፊት መድኃኒት ከተጀመረ ሊቋረጥ እንደማይችል አስጠንቅቀዋል። በየጊዜው ክትትል ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በሂደት እንደ ግፊቱ ሁኔታ መድኃኒቶች ሊቀነሱም ሊጨመሩም እንደሚችሉ አመላክተዋል። · የመስፋፋት ደረጃ የዓለም ጤና ድርጅት በ2024 ያወጣውን መረጃ ዋቢ አድርገው፤ 1/3ኛው የዓለም ሕዝቦች በደም ግፊት እንደሚጠቁ ዶክተር ሞላወርቅ አንስተዋል። ከእነዚህ መካከልም፤ 7 ነጥብ 6 ሚሊየን ገደማው በአንድም በሌላም ምክንያት ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ጠቁመዋል። አብዛኞቹ የደም ግፊት ታማሚዎች ቁጥር የሚመዘገበው ደግሞ በመካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ሀገራችንን ያካትታል ሲሉ ገልጸዋል። በሀገራችን ደረጃም ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ባይኖሩም ከግፊት ጋር በተያያዘ በ2001 ላይ በ35 ሳይቶች የተጠኑ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከ21 እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ በደም ግፊት የሚጠቃ ነው ይላሉ። በአብዛኛው ደግሞ ከተማ ላይ እንደሚበዛ ጠቁመው፤ በተለይም አዲስ አበባ ላይ እስከ 30 በመቶ እንደሚደርስ የጥናቶቹ ውጤቶች ማመላከታቸውን ተናግረዋል። አብዛኞቹ ኬዞች ደግሞ ዕድሜያቸው ከፍ ያለ፣ ክብደታቸው የጨመረ፣ አልኮል እና ሲጋራ የሚጠቀሙ እና የስኳር ህመም ያለባቸው ሰዎች ጋር የሚገናኙ መሆናቸውን አስረድተዋል። እንደ ዓለም አቀፍ ደረጃም ኬዙ ካለባቸው መካከል ግማሽ ያህሉ ግፊት እንዳለባቸው እንኳን እንደማያውቁ ነው የሚገልጹት። ለግፊት ሕክምና ትክክለኛ ክትትል አድርገው ግፊታቸውን በአግባቡ የሚቆጣጠሩት ከ 5 ሰዎች 1 መሆኑንም ጥናቶች ያሳያሉ ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ በሀገራችን በሕብረተሰቡ ዘንድ ለደም ግፊት መለካት ኬዙ ከተገኘም የሕክምና ክትትል የማድረግ ሁኔታዎች ዝቅተኛ መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ሕብረተሰቡ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከአካል ጉዳት እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል ተገንዝቦ፤ የደም ግፊቱን የመለካት ልምምዱን ሊያዳብር እንደሚገባ ዶክተር ሞላወርቅ መክረዋል። በሌላ በኩል እንደ ሀገራችን ባሉ ሆስፒታሎች በጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ ወይም መቋረጥ (ስትሮክ) ካለባቸው ሰዎች ከ70 እስከ 85 በመቶው ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ የሚከሰት መሆኑን ገልጸው፤ ድንገተኛ ግፊት መጨመር ከልብ እና ከደም ሥሮች ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዓለምም ሆነ እንደ ሀገር አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንደኛው ግፊት መሆኑንም አረጋግጠዋል። ስለዚህ የደም ግፊትን መለካት፣ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል፣ ከሱስ መራቅ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር ለጤናማ ሕይወት ከፍተኛ ሚና እንዳለው መክረዋል።  
 ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 5989
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 3712
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ‎ ‎​ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። ‎ ‎መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ‎ ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 13461
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 7486
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 13261
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 11720
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 79013
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 64168
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 44535
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 42110
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 32622
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 32071
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 31542
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 30832
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 79013
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 64168
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 44535
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 42110
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 6516
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 6435
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም