ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ የግብርና ምርቷን ለማሳደግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ነው
Aug 21, 2026 44
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ የግብርና ልማትን ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ በመስኖ ልማት፣ በተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችና በግብርና ሜካናይዜሽን ላይ በትኩረት እየሰራች መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት አምባሳደሮች ኮሚቴና የኢጋድ ፓርላማ ፎረም በአግሪፉድ ሲስተም ዙሪያ በአዲስ አበባ ያዘጋጁት ከፍተኛ የልምድ ልውውጥ መድረክ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የግብርና ልማትን ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ በመስኖ ልማት፣ በተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችና በግብርና ሜካናይዜሽን ላይ በትኩረት እየሰራች ነው። የክላስተር እርሻ ልማት አርሶ አደሮች የግብዓት፣ የቴክኖሎጂ፣ የባለሙያ ምክክር አገልግሎትና የገበያ ትስስሮችን በተሻለ ሁኔታ እንዲያገኙ እያስቻለ መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም በአረንጓዴ ዐሻራ እና በሌማት ትሩፋት ተነሳሽነቶች የአካባቢ ጥበቃን፣ የግብርና ምርታማነትንና የቤተሰብ ምግብና የአመጋገብ ስርዓትን ለማሻሻል ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ተወካይና በድርጅቱ የውጭ አገልግሎት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ኦማር ጃማ የአግሪፉድ ሲስተም ለውጥ የካምፓላ የግብርና ልማት ቃል ኪዳንን ወደ ተግባር በማሸጋገር፣ በጠንካራ ፖሊሲ፣ የሕግ ማዕቀፍ፣ በጀትና ኢንቨስትመንት በመደገፍ እንደሚሳካ ጠቁመዋል። ሀገራቱ ለምግብ ዋስትና ችግር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ፣ ለዝቅተኛ ምርታማነትና ለውስን የገበያ ትስስር የተጋለጡ በመሆኑ፣ የግብርና ለውጥን ለማፋጠን አባል ሀገራት የተቀናጀ ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል። በመድረኩ የአግሪፉድ ሲስተም ልማትን ለማፋጠን የፖሊሲ ቅንጅትን፣ የግብርና ኢንቨስትመንትን፣ የቀጣናዊ ንግድ ትስስርንና የፓርላማ ክትትልን ማጠናከል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
የትግራይ ህዝብ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሚያደርስበትን የግፍና መከራ ለማስቆም ትግሉን ማጠናከር አለበት-የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ
Aug 21, 2026 58
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018(ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል ህዝብ ሕገወጡ የሕወሓት ቡድን በክልሉ እያደረሰበት ያለውን ግፍና መከራ ለማስቆም ትግሉን ማጠናከር እንዳለበት የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ ገለጹ። ቡድኑ ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር የጥፋት ጥምረት በመመስረት ሀገሪቷን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት ከዳረገበት እኩይ ተግባሩ ባለመታቀብ ዛሬም የባዕዳንን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ መሆኑንም ገልጸዋል። የትንሳኤ ሰባ አንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ህገ ወጡ የሕወሃት ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር የጥፋት ጥምረት መመስረት ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት ከዳረገበት እኩይ ተግባሩ የቀጠለ ተልዕኮ የማስፈጸም ሂደት ነው። ሕገ-ወጡ ቡድኑ "ፅምዶ" በሚል ስም ከሻዕቢያ የጥፋት ሀይል ጋር የፈጠረው የጥፋት ጥምረት ኢትዮጵያን ለማፍረስና ከዘላቂ ልማቷ ለማደናቀፍ የተወጠነ የባዕዳን ተልዕኮ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሕገ-ወጥ ቡድን ከምስረታው ጀምሮ የኢትዮጵያዊነት ሥነ-ልቦና የነበራቸውንና ድብቅ አጀንዳውን የተረዱ የትግራይ ተወላጆችን በማጥፋት እና በማስወገድ የፈጸማቸው እኩይ ተግባራቱ ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን አክለዋል። ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት እንድትጋለጥ ማድረጉ አስታውሰው፤ ሕገ-ወጥ ቡድኑ ከምስረታው ጀምሮ ለሀገርም ሆነ ለትግራይ ክልል ህዝብ ጥቅም መከበር ከመቆም ይልቅ ለባዕዳን ሀይሎች ተልዕኮ መገዛቱን ያሳያል ብለዋል። ይህ ሕገ-ወጥ የሕወሃት የጥፋት ቡድን ለሰሜኑ ጦርነት መቀስቀስ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚያም በኋላ የፕሪቶሪያውን ስምምነት መጣሱና የጥፋት መንገድ መከተሉ የህገ ወጥ ቡድኑን ለባዕዳን የመላላክ ተፈጥሯዊ ባህሪው መሆኑን እንደሚያሳዩ ተናግረዋል። ሻዕቢያን ጨምሮ ከሌሎች የጥፋት ቡድኖች ጋር ያልተቀደሰ ጥምረት መመስረቱ ኢትዮጵያ ዘላቂ ልማቷን እንዳታረጋግጥና አሁንም ሀገሪቷን ለማመስ የተዘረጋ የባዕዳን ፕሮጀክት አካል መሆኑንም አመልክተዋል። ሕገ-ወጥ የሕወሃት ቡድን የጥፋት ተልዕኮን ለመፈጸም "ፅምዶ" በሚል መጠሪያ ከሻዕቢያ መንግስት ጋር የፈጠረው ጥምረት ኢትዮጵያን ከልማቷ እና ከሰላሟ ወደ ኋላ ለማስቀረት የተወጠነ የባዕዳን ሀይሎች እኩይ ሴራ እንደሆነም ገልጸዋል። የውጭ ኃይሎችን ፍላጎት በትግራይ ክልል ወጣቶች መስዋዕትነት ለማስፈጸም የሚደረገው ጥረት፣ በህዝቡና በወጣቱ ንቃት ምክንያት እንደፈለገው ሊሳካ አለመቻሉን ተናግረዋል። ሕገ-ወጡ ህወሓት የላኪዎቹን ተልዕኮ ለመፈጸም ጥረት የሚያደርግ ቢሆንም፤ የትግራይ ክልል ህዝብ፣ ወጣቱና ምሁራኑ ከቡድኑ ትክክለኛ ማንነት ከየትኛውም ጊዜ በላይ አሁን ላይ መረዳታቸውን ጠቁመዋል። በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የሚኖሩ ትግራይ ክልል ተወላጆች ይበልጥ በመደራጀትና በመተጋገዝ ለቀውሱ ምክንያት የሆነውን አካል በፍጥነት በማስወገድ ረገድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ በውጭ ሀገር የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆችም አስፈላጊውን ተፅዕኖ በማሳደር ቡድኑ እያደረሰ ያለውን ግፍና መከራ ለማስቆም መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል ተመናምኖ የነበረው የደን ሽፋን በአረንጓዴ አሻራ አማካኝነት በፍጥነት እያደገ ነው
Aug 21, 2026 69
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተከናወኑ ተግባራት አማካኝነት ተመናምኖ የነበረው የደን ሽፋን መልሶ እድገት እያሳየ መሆኑን የክልሉ ደን እና ዱር እንስሳት ድርጅት አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል ሰፊ የተፈጥሮ ሀብትና ብዝሃ-ሕይወት ባለቤት ቢሆንም፣ ባለፉት አሥርተ ዓመታት በሕገ-ወጥ የደን ምንጣሮ፣ ለእንጨትና ከሰል ምርት በሚደረግ ጭፍጨፋ እና ለእርሻ መሬት ማስፋፊያ ምክንያት የደን ሽፋኑ በከፍተኛ ደረጃ ተመናምኖ ቆይቷል። ይህ የደን ውድመት አካባቢውን ለአፈር መሸርሸር፣ ለወንዞችና ሐይቆች መድረቅ እንዲሁም ለምርታማነት መቀነስ ዳርጎት የነበረ ሲሆን፣ በተለይም እንደ ሐረማያ ባሉ አካባቢዎች የነበሩ የውሃ አካላት ሙሉ በሙሉ እስከመድ ረቅ ደርሰው የነበረው አካባቢያዊ ሥነ-ምህዳሩ ለከፍተኛ አደጋ ተጋልጦ ስለነበር ነው። ይህንን ሥነ-ምህዳራዊና ምጣኔ-ሀብታዊ አደጋ ለመቀልበስ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢኒሼቲቭ በሀገር ደረጃ እየተካሄደ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉም በየዓመቱ እንደ ዋነኛ መፍትሔ ተወስዶ ሰፊ የተቀናጀ ንቅናቄ በማካሄድ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ውጤት እየመጣ ነው። የኦሮሚያ ክልል ደን እና ዱር እንስሳት ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ አራርሳ ረጋሳ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በክልሉ ባለፉት ዓመታት የደን ሽፋኑን ለማሳደግ የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል። በክልሉ የደን ሽፋኑን ለማሳደግ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል፣ በተለይም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተራቁተው በነበሩ ቦታዎች ላይ ሳይንሳዊ መንገድን በተከተለ መልኩ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ጎን ለጎን አካባቢዎችን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ እንዲሁም ሕገ-ወጥ የእርሻ መሬት ማስፋፋትን ለመግታት በተሠራው ሥራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። በተለይም ችግኞችን በመትከል ላይ ብቻ ሳይወሰን ለእንክብካቤያቸው ከፍተኛ ትኩረት በመሰጠቱ ለውጤቱ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም በክልሉ ከዚህ በፊት ተመናምኖ የነበረው የደን ሽፋን ወደ 27 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ይህ የተቀናጀ ጥረት የአፈር መንሸራሸርን መከላከል፣ የአፈር ለምነትን መመለስ እንዲሁም የደረቁ ምንጮች፣ ሀይቆችና ወንዞች እንደገና እንዲጎለብቱ ያደረገ ሲሆን፣ በዚህም በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ደርቆ የነበረው የሐረማያ ሀይቅ ሙሉ በሙሉ ማገገሙን ለአብነት አንስተዋል። በአጠቃላይ የመርሃ ግብሩ ስኬት በሁሉም ወቅቶች መሬትን በማልማት፣ የአካባቢ ጥበቃን ከግብርና ስራዎች ጋር በማጣመር የምርትና ምርታማነት እድገትን ከማሳደግ አንጻር ከፍተኛ ድርሻ እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል። አቶ አራርሳ እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት በክልሉ በአጠቃላይ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በደን መልማቱን ገልጸዋል። ከአጠቃላይ መሬቱ ውስጥ 1 ሚሊዮን ሄክታር ያህሉ ለዱር እንስሳት እንክብካቤና ጥበቃ፣ ለፓርኮች፣ ለስፖርት ስፍራዎች ሲሆኑ፣ 700 ሺህ ሄክታር መሬት ደግሞ ለችግኝ ተከላ እና ለሰው ሰራሽ ደን ልማት የተመደበ ስፍራ ነው። ከአጠቃላይ መሬቱ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ደግሞ ሙሉ በሙሉ በተፈጥሮ ደን የተሸፈነ መሆኑን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ በማህበረሰብ አቀፍ እና አማራጭ የፍትሕ ስርዓቶችን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ አብነት የሚሆን ስራ እያከናወነች ነው -በኔዘርላንድስ ሄግ የሚገኘው የሕግ ፈጠራ ተቋም
Aug 21, 2026 64
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አማራጭ ሀገር በቀል የክርክር መፍቻ ስልቶችን ወደ ማህበረሰቡ በማቅረብ የፍትሕ ስርዓቷን ለማሻሻል የምታደርገው ጥረት በአብነት የሚጠቀስ መሆኑን ተቀማጭነቱን በኔዘርላንድስ ሄግ ያደረገው የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) አስታወቀ። የተቋሙ ዋና ኦፕሬቲንግ ኦፊሰር ሼካር ፑላ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥ ኢትዮጵያ የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከላትን (CJCs) ተደራሽነት እያሰፋችበት ያለችበትን መንገድ እና የሀገር ሽማግሌዎችን በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ለማካተት የምታደርገውን ጥረት አድንቀዋል። ይህ አማራጭ የበለጠ ተደራሽ፣ ቀልጣፋ እና ሰላማዊ የፍትሕ ስርዓትን ለመገንባት የሚያስችል ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በማህበረሰባዊ የፍትሕ አማራጭ እና አዳዲስ የፍትሕ መስጫ መንገዶች በእርግጥም ከግንባር ቀደም ሀገራት አንዷ ናት ብለዋል። የፍትሕ ሚኒስቴር ከአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች እና ህዝብን ማዕከል ካደረገ የፍትሕ አሰራር ጋር በተያያዘ ላሳየው ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ አመርቂ ስራ እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ መልካም ተሞክሮዎችን እየቀሰመች ልምዷን ለሌሎች ሀገራት የማካፈል ትልቅ አቅም እንዳላት አንስተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት በሲዳማ ክልል የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከል በተከፈተበት ወቅት ያደረጉትን ጉብኝት በማስታወስ፣ የፍትሕ ስርዓቱ ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር ያለውን አዎንታዊ ግንኙነት አድንቀዋል። በጉብኝታቸው የፍትሕ ሚኒስቴር ለባህላዊ መሪዎች ያለውን አክብሮት ለመመልከት መቻላቸውንና ዘመናትን ያስቆጠሩ የማህበረሰብ አቀፍ የክርክር መፍቻ ልምዶቻቸው ከመደበኛው የፍትሕ ስርዓት ጎን ለጎን እንዴት መስራት እንደሚችሉ መመሪያ መስጠቱን አውስተዋል። ይህ የፍትሕ አማራጭ ትልቅ ተስፋ ያለው፣ ሊሰፋ የሚችል እና ወደፊት ኢትዮጵያን በጥሩ ሁኔታ ሊጠቅም የሚችል አሰራር ነው ብለዋል። መደበኛ ያልሆነ የፍትሕ አሰጣጥ ስርዓት አለመግባባቶችን በፍጥነት ለመፍታት እና የበለጠ ሰላማዊ ማህበረሰብ ለመገንባት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ጠቁመዋል። ይህ አማራጭ ህዝቡ ወደ ዋና ዋና ከተሞች ወይም ወደ ሩቅ ፍርድ ቤቶች ከመጓዝ ይልቅ ባለበት ማህበረሰብ ውስጥ ፍትህን በቅርበት ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል። ለባህላዊ መሪዎች የተዘጋጁ መመሪያዎች የማህበረሰብ እሴቶችን በጠበቀ መልኩ፣ አለመግባባቶችን በመፍታት ረገድ የበለጠ ወጥ እና መረጃን መሰረት ያደረጉ አማራጮችን በማሳደግ ስርዓቱን የበለጠ ሊያጠናክሩት እንደሚችሉ ተናግረዋል። ለኢትዮጵያ የፍትሕ ማሻሻያ ጥረቶች ማዕከል የሆነው እ.አ.አ. በ2019 የተካሄደው የፍትሕ ፍላጎት እና እርካታ ጥናት መሆኑን ጠቅሰው፤ ጥናቱ በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን ለመለየት የረዳ እና ህዝብን ማዕከል ያደረጉ ማሻሻያዎች ላይ አስፈላጊ መሰረት የጣለ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አውስተዋል። ጥናቱ የፍትሕ አገልግሎቶችን በዜጎች እውነተኛ ፍላጎቶች እና ተሞክሮዎች ዙሪያ የመቅረፅን አስፈላጊነት ያሳየ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል። በብዙ ሀገራት እንሰራለን፤ በፍትሕ ሚኒስቴር በኩል ያለው ቁርጠኝነት ግን አርአያነት ያለው ነው ብለዋል። የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት እ.ኤ.አ. በ2019 ከቀድሞው ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመበት ጊዜ አንስቶ የዘለቀ ነው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ተቋሙ በሲዳማ እና አፋር ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በሌሎች አካባቢዎች የመደበኛ ፍትሕ ተቋማትን ማህበረሰብ አቀፍ እና ባህላዊ አሰራሮች ጋር የማስተሳሰር ስራን እንዲሁም የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከላትን ሲደግፍ ቆይቷል። ይህ እንቅስቃሴ ፍትህን ተደራሽ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን፣ በተለይም በቦታ፣ በፋይናንስ ወይም በተቋማት ምክንያት ለመደበኛ ፍርድ ቤቶች ተደራሽ ያልሆኑ ዜጎች ምላሽ ሰጪ ለማድረግ የሚደረገውን ሰፊ ጥረት የሚያንጸባርቅ ነው። የፍትሕ አገልግሎቶችን ወደ ማህበረሰቡ በማቅረብ እና ባህላዊ ተቋማት በግልጽ ማዕቀፍ ውስጥ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበትን እድል በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ የካበቱ የማህበረሰብ ልምዶችን ከዘመናዊ የፍትሕ አማራጮች ጋር ለማዋሃድ እየሰራች ይገኛል። ይህም ኢትዮጵያ የቆዩ ቅሬታዎችን ለመፍታት፣ ማህበራዊ ትስስርን ለማጠናከር እና አለመግባባቶችን ለመፍታት የበለጠ ሰላማዊ የአሰራር ዘዴዎችን ለመገንባት እንዲሁም የሽግግር ፍትሕ ሂደት እና የሀገራዊ የምክክር ስራዎችን እያከናወነች ባለችበት በአሁኑ ወቅት የመጣ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ለሄግ የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) የኢትዮጵያ ተሞክሮ ከሀገሪቷ ባሻገር ለሌሎች ሀገራት መልካም ትምህርቶችን የሚሰጥ መሆኑን ኦፊሰሩ ተናግረዋል።
በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው
Aug 21, 2026 74
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018(ኢዜአ) ፦ በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ተግባራዊ መገለጫ መሆኑንም አቶ ጌቱ ተናግረዋል።   የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትና ኢኒሼቲቮችን አፈፃፀም በገመገመበት ወቅት አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት አምጥተዋል። በተለይ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና ተጠቃሚነትን ለሚያረጋግጡ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል። በዚህም የአረጋውያንና አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እድሳትና መልሶ ግንባታ፣ የአካባቢ ንጽህና ጥበቃ፣ ችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ፣ የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠትና የትምህርት ቁሳ ቁስ ድጋፍ የማሰባሰብ ስራዎች መጠናከራቸውን ቀጥለዋል።   የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ማሳያ ነው ያሉት ኃላፊው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በሌላ በኩል አመራሩ ለፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ እና የ 7 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና ልዩ ትኩረት በመስጠት እንዲሰራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በክልሉ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተጀመሩ የቅዳሜ ገበያዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ገልፀዋል።
የሚታይ
ኢትዮጵያ የግብርና ምርቷን ለማሳደግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ነው
Aug 21, 2026 44
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ የግብርና ልማትን ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ በመስኖ ልማት፣ በተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችና በግብርና ሜካናይዜሽን ላይ በትኩረት እየሰራች መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት አምባሳደሮች ኮሚቴና የኢጋድ ፓርላማ ፎረም በአግሪፉድ ሲስተም ዙሪያ በአዲስ አበባ ያዘጋጁት ከፍተኛ የልምድ ልውውጥ መድረክ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የግብርና ልማትን ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ በመስኖ ልማት፣ በተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችና በግብርና ሜካናይዜሽን ላይ በትኩረት እየሰራች ነው። የክላስተር እርሻ ልማት አርሶ አደሮች የግብዓት፣ የቴክኖሎጂ፣ የባለሙያ ምክክር አገልግሎትና የገበያ ትስስሮችን በተሻለ ሁኔታ እንዲያገኙ እያስቻለ መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም በአረንጓዴ ዐሻራ እና በሌማት ትሩፋት ተነሳሽነቶች የአካባቢ ጥበቃን፣ የግብርና ምርታማነትንና የቤተሰብ ምግብና የአመጋገብ ስርዓትን ለማሻሻል ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ተወካይና በድርጅቱ የውጭ አገልግሎት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ኦማር ጃማ የአግሪፉድ ሲስተም ለውጥ የካምፓላ የግብርና ልማት ቃል ኪዳንን ወደ ተግባር በማሸጋገር፣ በጠንካራ ፖሊሲ፣ የሕግ ማዕቀፍ፣ በጀትና ኢንቨስትመንት በመደገፍ እንደሚሳካ ጠቁመዋል። ሀገራቱ ለምግብ ዋስትና ችግር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ፣ ለዝቅተኛ ምርታማነትና ለውስን የገበያ ትስስር የተጋለጡ በመሆኑ፣ የግብርና ለውጥን ለማፋጠን አባል ሀገራት የተቀናጀ ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል። በመድረኩ የአግሪፉድ ሲስተም ልማትን ለማፋጠን የፖሊሲ ቅንጅትን፣ የግብርና ኢንቨስትመንትን፣ የቀጣናዊ ንግድ ትስስርንና የፓርላማ ክትትልን ማጠናከል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
የትግራይ ህዝብ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሚያደርስበትን የግፍና መከራ ለማስቆም ትግሉን ማጠናከር አለበት-የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ
Aug 21, 2026 58
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018(ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል ህዝብ ሕገወጡ የሕወሓት ቡድን በክልሉ እያደረሰበት ያለውን ግፍና መከራ ለማስቆም ትግሉን ማጠናከር እንዳለበት የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ ገለጹ። ቡድኑ ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር የጥፋት ጥምረት በመመስረት ሀገሪቷን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት ከዳረገበት እኩይ ተግባሩ ባለመታቀብ ዛሬም የባዕዳንን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ መሆኑንም ገልጸዋል። የትንሳኤ ሰባ አንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ህገ ወጡ የሕወሃት ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር የጥፋት ጥምረት መመስረት ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት ከዳረገበት እኩይ ተግባሩ የቀጠለ ተልዕኮ የማስፈጸም ሂደት ነው። ሕገ-ወጡ ቡድኑ "ፅምዶ" በሚል ስም ከሻዕቢያ የጥፋት ሀይል ጋር የፈጠረው የጥፋት ጥምረት ኢትዮጵያን ለማፍረስና ከዘላቂ ልማቷ ለማደናቀፍ የተወጠነ የባዕዳን ተልዕኮ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሕገ-ወጥ ቡድን ከምስረታው ጀምሮ የኢትዮጵያዊነት ሥነ-ልቦና የነበራቸውንና ድብቅ አጀንዳውን የተረዱ የትግራይ ተወላጆችን በማጥፋት እና በማስወገድ የፈጸማቸው እኩይ ተግባራቱ ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን አክለዋል። ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት እንድትጋለጥ ማድረጉ አስታውሰው፤ ሕገ-ወጥ ቡድኑ ከምስረታው ጀምሮ ለሀገርም ሆነ ለትግራይ ክልል ህዝብ ጥቅም መከበር ከመቆም ይልቅ ለባዕዳን ሀይሎች ተልዕኮ መገዛቱን ያሳያል ብለዋል። ይህ ሕገ-ወጥ የሕወሃት የጥፋት ቡድን ለሰሜኑ ጦርነት መቀስቀስ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚያም በኋላ የፕሪቶሪያውን ስምምነት መጣሱና የጥፋት መንገድ መከተሉ የህገ ወጥ ቡድኑን ለባዕዳን የመላላክ ተፈጥሯዊ ባህሪው መሆኑን እንደሚያሳዩ ተናግረዋል። ሻዕቢያን ጨምሮ ከሌሎች የጥፋት ቡድኖች ጋር ያልተቀደሰ ጥምረት መመስረቱ ኢትዮጵያ ዘላቂ ልማቷን እንዳታረጋግጥና አሁንም ሀገሪቷን ለማመስ የተዘረጋ የባዕዳን ፕሮጀክት አካል መሆኑንም አመልክተዋል። ሕገ-ወጥ የሕወሃት ቡድን የጥፋት ተልዕኮን ለመፈጸም "ፅምዶ" በሚል መጠሪያ ከሻዕቢያ መንግስት ጋር የፈጠረው ጥምረት ኢትዮጵያን ከልማቷ እና ከሰላሟ ወደ ኋላ ለማስቀረት የተወጠነ የባዕዳን ሀይሎች እኩይ ሴራ እንደሆነም ገልጸዋል። የውጭ ኃይሎችን ፍላጎት በትግራይ ክልል ወጣቶች መስዋዕትነት ለማስፈጸም የሚደረገው ጥረት፣ በህዝቡና በወጣቱ ንቃት ምክንያት እንደፈለገው ሊሳካ አለመቻሉን ተናግረዋል። ሕገ-ወጡ ህወሓት የላኪዎቹን ተልዕኮ ለመፈጸም ጥረት የሚያደርግ ቢሆንም፤ የትግራይ ክልል ህዝብ፣ ወጣቱና ምሁራኑ ከቡድኑ ትክክለኛ ማንነት ከየትኛውም ጊዜ በላይ አሁን ላይ መረዳታቸውን ጠቁመዋል። በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የሚኖሩ ትግራይ ክልል ተወላጆች ይበልጥ በመደራጀትና በመተጋገዝ ለቀውሱ ምክንያት የሆነውን አካል በፍጥነት በማስወገድ ረገድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ በውጭ ሀገር የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆችም አስፈላጊውን ተፅዕኖ በማሳደር ቡድኑ እያደረሰ ያለውን ግፍና መከራ ለማስቆም መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በማህበረሰብ አቀፍ እና አማራጭ የፍትሕ ስርዓቶችን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ አብነት የሚሆን ስራ እያከናወነች ነው -በኔዘርላንድስ ሄግ የሚገኘው የሕግ ፈጠራ ተቋም
Aug 21, 2026 64
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አማራጭ ሀገር በቀል የክርክር መፍቻ ስልቶችን ወደ ማህበረሰቡ በማቅረብ የፍትሕ ስርዓቷን ለማሻሻል የምታደርገው ጥረት በአብነት የሚጠቀስ መሆኑን ተቀማጭነቱን በኔዘርላንድስ ሄግ ያደረገው የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) አስታወቀ። የተቋሙ ዋና ኦፕሬቲንግ ኦፊሰር ሼካር ፑላ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥ ኢትዮጵያ የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከላትን (CJCs) ተደራሽነት እያሰፋችበት ያለችበትን መንገድ እና የሀገር ሽማግሌዎችን በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ለማካተት የምታደርገውን ጥረት አድንቀዋል። ይህ አማራጭ የበለጠ ተደራሽ፣ ቀልጣፋ እና ሰላማዊ የፍትሕ ስርዓትን ለመገንባት የሚያስችል ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በማህበረሰባዊ የፍትሕ አማራጭ እና አዳዲስ የፍትሕ መስጫ መንገዶች በእርግጥም ከግንባር ቀደም ሀገራት አንዷ ናት ብለዋል። የፍትሕ ሚኒስቴር ከአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች እና ህዝብን ማዕከል ካደረገ የፍትሕ አሰራር ጋር በተያያዘ ላሳየው ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ አመርቂ ስራ እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ መልካም ተሞክሮዎችን እየቀሰመች ልምዷን ለሌሎች ሀገራት የማካፈል ትልቅ አቅም እንዳላት አንስተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት በሲዳማ ክልል የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከል በተከፈተበት ወቅት ያደረጉትን ጉብኝት በማስታወስ፣ የፍትሕ ስርዓቱ ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር ያለውን አዎንታዊ ግንኙነት አድንቀዋል። በጉብኝታቸው የፍትሕ ሚኒስቴር ለባህላዊ መሪዎች ያለውን አክብሮት ለመመልከት መቻላቸውንና ዘመናትን ያስቆጠሩ የማህበረሰብ አቀፍ የክርክር መፍቻ ልምዶቻቸው ከመደበኛው የፍትሕ ስርዓት ጎን ለጎን እንዴት መስራት እንደሚችሉ መመሪያ መስጠቱን አውስተዋል። ይህ የፍትሕ አማራጭ ትልቅ ተስፋ ያለው፣ ሊሰፋ የሚችል እና ወደፊት ኢትዮጵያን በጥሩ ሁኔታ ሊጠቅም የሚችል አሰራር ነው ብለዋል። መደበኛ ያልሆነ የፍትሕ አሰጣጥ ስርዓት አለመግባባቶችን በፍጥነት ለመፍታት እና የበለጠ ሰላማዊ ማህበረሰብ ለመገንባት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ጠቁመዋል። ይህ አማራጭ ህዝቡ ወደ ዋና ዋና ከተሞች ወይም ወደ ሩቅ ፍርድ ቤቶች ከመጓዝ ይልቅ ባለበት ማህበረሰብ ውስጥ ፍትህን በቅርበት ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል። ለባህላዊ መሪዎች የተዘጋጁ መመሪያዎች የማህበረሰብ እሴቶችን በጠበቀ መልኩ፣ አለመግባባቶችን በመፍታት ረገድ የበለጠ ወጥ እና መረጃን መሰረት ያደረጉ አማራጮችን በማሳደግ ስርዓቱን የበለጠ ሊያጠናክሩት እንደሚችሉ ተናግረዋል። ለኢትዮጵያ የፍትሕ ማሻሻያ ጥረቶች ማዕከል የሆነው እ.አ.አ. በ2019 የተካሄደው የፍትሕ ፍላጎት እና እርካታ ጥናት መሆኑን ጠቅሰው፤ ጥናቱ በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን ለመለየት የረዳ እና ህዝብን ማዕከል ያደረጉ ማሻሻያዎች ላይ አስፈላጊ መሰረት የጣለ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አውስተዋል። ጥናቱ የፍትሕ አገልግሎቶችን በዜጎች እውነተኛ ፍላጎቶች እና ተሞክሮዎች ዙሪያ የመቅረፅን አስፈላጊነት ያሳየ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል። በብዙ ሀገራት እንሰራለን፤ በፍትሕ ሚኒስቴር በኩል ያለው ቁርጠኝነት ግን አርአያነት ያለው ነው ብለዋል። የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት እ.ኤ.አ. በ2019 ከቀድሞው ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመበት ጊዜ አንስቶ የዘለቀ ነው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ተቋሙ በሲዳማ እና አፋር ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በሌሎች አካባቢዎች የመደበኛ ፍትሕ ተቋማትን ማህበረሰብ አቀፍ እና ባህላዊ አሰራሮች ጋር የማስተሳሰር ስራን እንዲሁም የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከላትን ሲደግፍ ቆይቷል። ይህ እንቅስቃሴ ፍትህን ተደራሽ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን፣ በተለይም በቦታ፣ በፋይናንስ ወይም በተቋማት ምክንያት ለመደበኛ ፍርድ ቤቶች ተደራሽ ያልሆኑ ዜጎች ምላሽ ሰጪ ለማድረግ የሚደረገውን ሰፊ ጥረት የሚያንጸባርቅ ነው። የፍትሕ አገልግሎቶችን ወደ ማህበረሰቡ በማቅረብ እና ባህላዊ ተቋማት በግልጽ ማዕቀፍ ውስጥ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበትን እድል በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ የካበቱ የማህበረሰብ ልምዶችን ከዘመናዊ የፍትሕ አማራጮች ጋር ለማዋሃድ እየሰራች ይገኛል። ይህም ኢትዮጵያ የቆዩ ቅሬታዎችን ለመፍታት፣ ማህበራዊ ትስስርን ለማጠናከር እና አለመግባባቶችን ለመፍታት የበለጠ ሰላማዊ የአሰራር ዘዴዎችን ለመገንባት እንዲሁም የሽግግር ፍትሕ ሂደት እና የሀገራዊ የምክክር ስራዎችን እያከናወነች ባለችበት በአሁኑ ወቅት የመጣ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ለሄግ የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) የኢትዮጵያ ተሞክሮ ከሀገሪቷ ባሻገር ለሌሎች ሀገራት መልካም ትምህርቶችን የሚሰጥ መሆኑን ኦፊሰሩ ተናግረዋል።
የተወዳጁ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲስ የውድድር ዘመን በሻምፒዮኑ አርሰናል እና ኮቨንተሪ ሲቲ ጨዋታ ይጀመራል
Aug 21, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ጅማሮውን ያደርጋል። ምሽት አራት ሰዓት ላይ አርሰናል ከኮቨንተሪ ሲቲ ጋር በኤምሬትስ ስታዲየም ጨዋታውን ያደርጋል። አርሰናል የወቅቱ የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ነው። ተጋጣሚው ኮቨንተሪ ሲቲ ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ተመልሷል። ሁለቱ ቡድኖች በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሲገናኙ የአሁኑ ለ19ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 18 ጨዋታዎች አርሰናል 10ሩን በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ኮቨንተሪ ሲቲ ሦስት ጊዜ ሲያሸንፍ በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። አርሰናል በ18ቱ ጨዋታዎች ላይ 25 ጎሎችን ሲያስቆጥር ኮቨንተሪ ሲቲ 13 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሁለቱ ቡድኖች ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ የተገናኙት እ.አ.አ በ2001 ነበር። በወቅቱ ባደረጉት ጨዋታ አርሰናል በዴኒስ ቤርካምፕ ጎል 1 ለ 0 አሸንፏል። ኮቨንተሪ ሲቲ በዛው ዓመት ከሊጉ ወርዷል። ኮቨንተሪ በፍራንክ ላምፓርድ እየተመራ በሻምፒዮንሺፑ በ95 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ተመልሷል። በማይክል አርቴታ የሚመራው አርሰናል የሻምፒዮንነት ክብሩን የማስጠበቅ ጉዞውን ከአዲስ አዳጊው ክለብ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ይጀምራል። ኮቨንተሪ ሲቲ በመጀመሪያው የሊግ ጨዋታው ከሊጉ የወቅቱ የዋንጫ ባለቤት ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል። የ36 ዓመቱ ቶም ብራሞል የመክፈቻውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመራሉ። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሔ ለማበጀት ትልቅ ዕድል የፈጠረው-ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ
Aug 21, 2026 76
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሔ በማበጀት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ተመካካሪዎች ገለጹ። ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወደ ማጠቃለያ ምዕራፍ ደርሷል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ረዳት ፕሮፌሰር አብዱልወኪል ሀሰን ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደገለጹት፥ ምክክሩ የአሳታፊነት መርሆዎችን በጠበቀ መልኩ እየተካሄደ ነው። ለምክክር በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት ያንሸራሸረበት መሆኑን ጠቁመዋል። ለነገዋ የተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ጥሩ ልምድ መሆኑን ተናግረዋል። ምክክሩ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸው፤ ምክክር ለችግሮች መፍቻ ቁልፍ መሆኑን አመልክተዋል። ሌላዋ ተመካካሪ ዓለምፀሐይ ተስፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በምክክሩ በተደረጉ የቡድን ውይይቶች የተለያዩ ሀሳቦች በሚገባ የተንሸራሸሩ መሆኑን ገልጸዋል። "ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት ነው፤ እዚህ የተሰባሰብነውም ዘላቂ ሰላም የመገንባት ሀገራዊ ውጥን ውጤታማ እንዲሆን መሰረት ለማኖር ነው" ብለዋል። ምክክሩ የኢትዮጵያን ቋጠሮዎች ለመፍታት ሁነኛ መንገድ በመሆኑ በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ በመሳተፌም እጅግ ደስተኛ ነኝ ብለዋል። በምክክሩ ላይ ለኢትዮጵያ ይበጃሉ ያልናቸውን ሀሳቦች ሁሉ አቅርበናል ያሉት ደግሞ ሌላው የምክክሩ ተሳታፊ አሳምነው ዋቅጅራ (ዶ/ር) ናቸው። የምክክር መድረኩ ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵያን ያማከለና ሁሉንም አካታች ያደረገ ጥሩ ውይይት የተካሄደበት መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፤ በአጠቃላይ ድምር ውጤቱም ሀገርን የሚያሻግሩ ውጤቶችን እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የትግራይ ህዝብ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሚያደርስበትን የግፍና መከራ ለማስቆም ትግሉን ማጠናከር አለበት-የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ
Aug 21, 2026 58
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018(ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል ህዝብ ሕገወጡ የሕወሓት ቡድን በክልሉ እያደረሰበት ያለውን ግፍና መከራ ለማስቆም ትግሉን ማጠናከር እንዳለበት የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ ገለጹ። ቡድኑ ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር የጥፋት ጥምረት በመመስረት ሀገሪቷን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት ከዳረገበት እኩይ ተግባሩ ባለመታቀብ ዛሬም የባዕዳንን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ መሆኑንም ገልጸዋል። የትንሳኤ ሰባ አንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ህገ ወጡ የሕወሃት ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር የጥፋት ጥምረት መመስረት ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት ከዳረገበት እኩይ ተግባሩ የቀጠለ ተልዕኮ የማስፈጸም ሂደት ነው። ሕገ-ወጡ ቡድኑ "ፅምዶ" በሚል ስም ከሻዕቢያ የጥፋት ሀይል ጋር የፈጠረው የጥፋት ጥምረት ኢትዮጵያን ለማፍረስና ከዘላቂ ልማቷ ለማደናቀፍ የተወጠነ የባዕዳን ተልዕኮ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሕገ-ወጥ ቡድን ከምስረታው ጀምሮ የኢትዮጵያዊነት ሥነ-ልቦና የነበራቸውንና ድብቅ አጀንዳውን የተረዱ የትግራይ ተወላጆችን በማጥፋት እና በማስወገድ የፈጸማቸው እኩይ ተግባራቱ ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን አክለዋል። ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት እንድትጋለጥ ማድረጉ አስታውሰው፤ ሕገ-ወጥ ቡድኑ ከምስረታው ጀምሮ ለሀገርም ሆነ ለትግራይ ክልል ህዝብ ጥቅም መከበር ከመቆም ይልቅ ለባዕዳን ሀይሎች ተልዕኮ መገዛቱን ያሳያል ብለዋል። ይህ ሕገ-ወጥ የሕወሃት የጥፋት ቡድን ለሰሜኑ ጦርነት መቀስቀስ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚያም በኋላ የፕሪቶሪያውን ስምምነት መጣሱና የጥፋት መንገድ መከተሉ የህገ ወጥ ቡድኑን ለባዕዳን የመላላክ ተፈጥሯዊ ባህሪው መሆኑን እንደሚያሳዩ ተናግረዋል። ሻዕቢያን ጨምሮ ከሌሎች የጥፋት ቡድኖች ጋር ያልተቀደሰ ጥምረት መመስረቱ ኢትዮጵያ ዘላቂ ልማቷን እንዳታረጋግጥና አሁንም ሀገሪቷን ለማመስ የተዘረጋ የባዕዳን ፕሮጀክት አካል መሆኑንም አመልክተዋል። ሕገ-ወጥ የሕወሃት ቡድን የጥፋት ተልዕኮን ለመፈጸም "ፅምዶ" በሚል መጠሪያ ከሻዕቢያ መንግስት ጋር የፈጠረው ጥምረት ኢትዮጵያን ከልማቷ እና ከሰላሟ ወደ ኋላ ለማስቀረት የተወጠነ የባዕዳን ሀይሎች እኩይ ሴራ እንደሆነም ገልጸዋል። የውጭ ኃይሎችን ፍላጎት በትግራይ ክልል ወጣቶች መስዋዕትነት ለማስፈጸም የሚደረገው ጥረት፣ በህዝቡና በወጣቱ ንቃት ምክንያት እንደፈለገው ሊሳካ አለመቻሉን ተናግረዋል። ሕገ-ወጡ ህወሓት የላኪዎቹን ተልዕኮ ለመፈጸም ጥረት የሚያደርግ ቢሆንም፤ የትግራይ ክልል ህዝብ፣ ወጣቱና ምሁራኑ ከቡድኑ ትክክለኛ ማንነት ከየትኛውም ጊዜ በላይ አሁን ላይ መረዳታቸውን ጠቁመዋል። በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የሚኖሩ ትግራይ ክልል ተወላጆች ይበልጥ በመደራጀትና በመተጋገዝ ለቀውሱ ምክንያት የሆነውን አካል በፍጥነት በማስወገድ ረገድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ በውጭ ሀገር የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆችም አስፈላጊውን ተፅዕኖ በማሳደር ቡድኑ እያደረሰ ያለውን ግፍና መከራ ለማስቆም መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሔ ለማበጀት ትልቅ ዕድል የፈጠረው-ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ
Aug 21, 2026 76
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሔ በማበጀት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ተመካካሪዎች ገለጹ። ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወደ ማጠቃለያ ምዕራፍ ደርሷል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ረዳት ፕሮፌሰር አብዱልወኪል ሀሰን ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደገለጹት፥ ምክክሩ የአሳታፊነት መርሆዎችን በጠበቀ መልኩ እየተካሄደ ነው። ለምክክር በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት ያንሸራሸረበት መሆኑን ጠቁመዋል። ለነገዋ የተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ጥሩ ልምድ መሆኑን ተናግረዋል። ምክክሩ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸው፤ ምክክር ለችግሮች መፍቻ ቁልፍ መሆኑን አመልክተዋል። ሌላዋ ተመካካሪ ዓለምፀሐይ ተስፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በምክክሩ በተደረጉ የቡድን ውይይቶች የተለያዩ ሀሳቦች በሚገባ የተንሸራሸሩ መሆኑን ገልጸዋል። "ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት ነው፤ እዚህ የተሰባሰብነውም ዘላቂ ሰላም የመገንባት ሀገራዊ ውጥን ውጤታማ እንዲሆን መሰረት ለማኖር ነው" ብለዋል። ምክክሩ የኢትዮጵያን ቋጠሮዎች ለመፍታት ሁነኛ መንገድ በመሆኑ በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ በመሳተፌም እጅግ ደስተኛ ነኝ ብለዋል። በምክክሩ ላይ ለኢትዮጵያ ይበጃሉ ያልናቸውን ሀሳቦች ሁሉ አቅርበናል ያሉት ደግሞ ሌላው የምክክሩ ተሳታፊ አሳምነው ዋቅጅራ (ዶ/ር) ናቸው። የምክክር መድረኩ ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵያን ያማከለና ሁሉንም አካታች ያደረገ ጥሩ ውይይት የተካሄደበት መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፤ በአጠቃላይ ድምር ውጤቱም ሀገርን የሚያሻግሩ ውጤቶችን እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በመከላከያ እና ደህንነት መስኮች ስትራቴጂካዊ ትብብር ለመመስረት ስምምነት ላይ ደረሱ
Aug 21, 2026 229
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 15 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በመከላከያ እና ደህንነት መስኮች ሁለንተናዊ ስትራቴጂካዊ ትብብር ለመመስረት ስምምነት ላይ ደርሰዋል። የአገር መከላከያ ሚኒስቴር የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ የተመራ ከፍተኛ ወታደራዊ ኃላፊዎችን ያካተተ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በአሜሪካ ከነሐሴ 13 እስከ 14/ 2018 ዓ.ም ጉብኝት በማድረግ በፔንታጎን ከአቻዎቻቸው እና ሌሎች ከፍተኛ የአሜሪካ ጦር ሚኒስቴር አመራሮች ጋር የሁለትዮሽ የጋራ ምክክሮች አድርገዋል። በዚህም በፔንታጎን የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ረዳት የመከላከያ ሚኒስትር ብራያን ጄ. ኤሊስ ጋር በጋራ በተመራ ምክክር የሁለቱን አገራት ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ትብብሮችን ወደ አዲስና የላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ከመግባባት ደርሰዋል። የሁለቱም አገራት የመከላከያ ተቋማት አመራሮች የተቋማቱን ትብብር ለማስፋት እና ስትራቴጂካዊ ቅንጅትን ይበልጥ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ስትራቴጂካዊ ትብብሩ ዘላቂ ብሔራዊ ጥቅምና የጋራ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፣የጋራ መተማመንን በማጠናከር ዘላቂ ትብብር መመስረት እና በአፍሪካ ቀንድ እና በሰፊው ቀጣና ዘላቂ ሰላም፣ ደህንነት እና መረጋጋትን ለማስፈን የጋራ ጥረቶችን ለማሳደግ ዓላማ በሚያደርግ ዋና ዋና ምሰሶዎች የሚመራ ነው። ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ እና ምክትል ረዳት ሚኒስትር ብራያን ጄ. ኤሊስ የተደረሱትን ማዕቀፎች በፍጥነት ወደ ተግባር ለማስገባት እና የሁለትዮሽ የመከላከያ ግንኙነቱን ወደ ተሻለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። በተጨማሪም ልዑካን ቡድኑ በቆይታው ወቅት ከሌሎች የአሜሪካ መከላከያ ተቋማት አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይቶችን ከማድረጉ ባሻገር ጉብኝቶችን ማካሄዱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ ታላቅነት ማሳያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ
Aug 20, 2026 353
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የኢትዮጵያን ታላቅነት ማሳያ ነው ሲሉ ወጣት ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተቃረበ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ወጣት ተመካካሪዎች የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሁሉም ተመካካሪ ድምጽ የተሰማበት እንዲሁም ኢትዮጵያ የራሷን ችግሮች በራሷ እየፈታች ያለችበት ትልቅ መድረክ ነው ብለዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ታረቀኝ በላቸው የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር መሆኗ ማሳያ ነው ሲል ገልጿል። ከሁሉም የማህበረሰቡ ክፍል የተወጣጡ ኢትዮጵያን ለጋራ መግባባት በአንድነት የተሰበሰቡበት መድረክ ነውም ብሏል። በምክክር ሂደቱም የማያግባቡ ነገሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችል ባህል የተገነባበት መሆኑን ነው ያስረዳው። ይህ የምክክር ሂደትም ለአፍሪካ ሀገራት ልምድ መቅሰም የሚችሉበት ነው ሲልም ተናግሯል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ወጣት ገነት መለሰው የምክክር ሂደቱ አካታች በመሆኑ እንደሀገር ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋገጥ እንደሚሆን ያላትን ተስፋ ገልጻለች። ምክክሩ ለሀገረ መንግስት ግንባታ በአንድነት የቆምንበት ነው ያለችው ደግሞ ሌላኛዋ ተመካካሪ ወጣት ፍቲ ሀሠን ነው። ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት በመሰለው መልኩ የሚገልጽበት ሁኔታ እና ለሀገራችን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ በጋራ መግባባት ላይ የደረስንበት ነውም ብላለች። ሌላኛዋ ተመካካሪ መድሃኒት ምትኩ እንደገለጸችው ታሪካዊ እና የመጀመሪያ የሆነው ይህ ምክክር አለመግባባቶችን በምክክር መፍታት እንዳለብን የሚያስገነዝብ መድረክ ነው።    
የአማራ ክልልን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ የጸጥታ ኃይሎች ኃላፊነታቸውን በላቀ ብቃት እየተወጡ ነው
Aug 20, 2026 359
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የአማራ ክልል የሚሊሽያና ሰላም አስከባሪ ሃይሎች የህዝቡን ሰላም በማስጠበቅ ኃላፊነታቸውን በብቃት እየተወጡ መሆኑን የክልሉ ሚሊሽያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ ገለጹ። ኮሚሽነሩ በክልሉ በጽንፈኞች ላይ የሚወሰደውን ህግ የማስከበር እርምጃና አጠቃላይ ሰላም በማስከበር ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም የክልሉ የሚሊሽያ እና ሌሎች የጸጥታ አካላት በቅንጅት የህዝቡን ሰላም በማስከበርና በጽንፈኞች ላይ እርምጃ በመውሰድ ህዝባዊ አደራና ኃላፊነታቸውን በላቀ ብቃት እየተወጡ ይገኛሉ ብለዋል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች በዘረፋ እና እገታ ተግባር ላይ የተሰማሩ ጽንፈኞችን ተከታትሎ እርምጃ የመውሰድ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል። የጽንፈኛ ቡድኑ ዓላማ ከህገ ወጡ ህወሃት እና ሌሎችም ባንዳዎች ጋር በመሆን ታሪካዊ የውጭ ጠላቶችን እኩይ አላማ ማሳካት መሆኑን አንስተው መንግስት ከየትኛውም ጊዜ በላይ ጠንካራ ህግ የማስከበር እርምጃ ይወስዳል ብለዋል። የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች "ጽምዶ" በሚል በመሰባሰብ የህዝብን ሰላም ለማወክ እየጣሩ መሆኑን ያነሱት ኮሚሽነሩ የፀጥታ ሃይላችን ከህዝቡ ጋር በመተባበር ሁሌም ሰላምን ለማስከበር የላቀ ዝግጁነት ላይ ነው ብለዋል። የክልሉን ሰላምና ፀጥታ በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የህዝቡ ድጋፍ፣ ትብብርና እገዛ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
ጉባኤው ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ሀሳብ እንድናዋጣ ዕድል ፈጥሮልናል - ተመካካሪዎች
Aug 20, 2026 360
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ሁላችንም ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ሀሳብ እንድናዋጣ ዕድል ፈጥሮልናል ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ ቆይቶ ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተቃረበ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ተመካካሪዎች መካከል ወጣት መርቀኒያ አሊ፣ ጉባኤው እጅግ ስኬታማ፣ አሳታፊ እና እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት የታየበት መሆኑን ተናግራለች። የምክክር ጉባኤው ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ሃሳብ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ጠቁማ፤ የምክክር ሂደቱ በመደማመጥ ለሀገር ግንባታ ሂደቱ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ የበሰሉ ሀሳቦች የመነጩበት ትልቅ ዕድል ነው ብላለች። መሰል ሀገራዊ የምክክር ሂደት ባህል ሆኖ እንዲቀጥል ከተደረገ የበለጸገችና ታላቅ ሀገር ለመገንባት ጥሩ መደላድል እንደሚፈጥርም ነው የገለጸችው። ይህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ሂደት እስካሁን ለቆዩት ችግሮች የጋራ መፍትሔ ከመስጠት ባለፈ ቀጣዩ ትውልድ ምክክርን ባህል እንዲያደርግ ጠንካራ መሰረት ጥሎ እንደሚያልፍ ተናግራለች። ሌላኛው ተመካካሪ ተረፈ ተከራይ በበኩሉ ሀገራዊ ምክክሩ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ሀሳብ እንድናዋጣ ዕድል ፈጥሮልናል ሲሉ ገልጸዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ቀደም ሲል በሀገሪቱ ለአለመግባባት መንስኤ የነበሩ ጉዳዮችን በጥልቀት ለመመርመር ዕድል የሰጠ ታሪክዊ ጉባኤ ነው ብለዋል። የምክክር ሂደቱ እኩል ሀሳብ የመስጠት ዕድል የተረጋገጠበትና አሳታፊ እንደነበርም ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደፊት የሚያራምዱና ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ግብዓት የሚሆኑ በሳል ሀሳቦች የተንሸራሸሩበት መሆኑን አብራርተዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው መደማመጥ ላይ የተመሰረተ የሀሳብ መዋጮ የተስተናገደበት በመሆኑ ለሀገር ለዘላቂ ሰላምና አንድነት መጠናከር መሰረት የሚጥል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ተመካካሪ ወይዘሮ ሃሊማ ሰይድ ናቸው። ጉባኤው ተመካካሪዎች የአንዱን ችግር እንደራሳቸው እንዲመለከቱ ዕድል በመፍጠር በጋራ የመፍትሔ ሀሳቦች የተመላከቱበት ጉባኤ እንደሆነ ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም የሚያመጣና የጋራ መግባባትን የሚያጎለብት መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል።
የምክክር ጉባኤው ሀገራዊ የምክክር ባህልን በማዳበር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል - ተመካካሪዎች
Aug 20, 2026 432
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የምክክር ባህልን በማዳበር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ ቆይቶ ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተቃረበ ይገኛል። ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ምክክሩ የሀገሪቱን ዘለቂ ሰላም፣ አንድነትና ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ መሠረት የሚጥል ነው። ምክክሩ በልዩነቶች መካከል የጋራ መግባባትን ለመፍጠር እና የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት አዲስ ምዕራፍ መክፈቱንም አስታውቀዋል። ተመካካሪ ካፒቴን ሰለሞን ግዛው እንደገለጹት፣ ምክክሩ የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላምና እድገት በጽኑ መሠረት ላይ ለመጣል የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለችና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ታላቅ ዕድል መሆኑን አስታውቀዋል። በምክክሩ ወቅት የላቀ የመተሳሰብና የሌሎችን ችግር እንደ ራስ የማየት ሂደት መታየቱን የጠቆሙት ካፒቴን ሰለሞን፣ የቡድን አደረጃጀቱም ሀሳብን በነፃነት ለማንሸራሸር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።   ሌላኛዋ ተመካካሪ ወይዘሮ ሰላም ዋቆ በበኩላቸው፣ ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮችን በምክክር መፍትሔ ማበጀት እንደሚቻል በተግባር የተረጋገጠበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። በምክክር ሂደቱ የሁሉም ተሳታፊዎች ሀሳብ ያለ ምንም ልዩነት በእኩልነት የተደመጠበት፣ የጋራ መከባበርና መግባባት የሰፈነበት እንደሆነም አብራርተዋል። ምክክሩ ከሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫዎችና ከውጭ ሀገራት የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጥላ ስር ተሰባስበው ሀገራቸውን ወደተሻለ ደረጃ ለማሻገር የመከሩበት ታሪካዊ መድረክ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሻለቃ ባሻ ተረፈ ወላኒ ናቸው።   የምክክር ሂደቱ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ያሳተፈና አካታች እንደነበር ያነሱት ሻለቃ ባሻ ተረፈ፣ መድረኩ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም፣ ወንድማማችነትና ሀገራዊ አንድነት እንዲጸና ለማድረግ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል። በምክክሩ ወቅት የታየው የመደማመጥና የመመካከር በጎ ልምድ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ሀገራዊ የፖለቲካና የማህበራዊ ባህል ሆኖ በዘላቂነት ሊቀጥል እንደሚገባም ጠቁመዋል።
ምክክሩ ዘላቂ ሰላምን ያሰፈነች ጠንካራ ሀገርን ለመገንባት የሚያስችል ሐሳብ እንደሚገኝበት ተስፋ እናደርጋለን-የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች
Aug 20, 2026 382
ሰመራ፣ነሀሴ 14/2018 (ኢዜአ)፡-ሃገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምን ያሰፈነች ጠንካራ ሀገርን ለመገንባት የሚያስችል ሐሳብ እንደሚገኝበት ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ዘመናትን ያስቆጠሩ ችግሮቻችንን በውይይት ለመፍታት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እየተካሄደ ያለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወደ ማጠቃለያ ምዕራፍ እየተቃረበ ነው። በምክክር መድረኩ ላይ ከመላው የሀገራችን ክፍሎችና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተወካዮችን ጨምሮ አራት ሺህ ተሳታፊዎች የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ በስምንት አጀንዳዎች ላይ በንቃት ሲሳተፉ ቆይተዋል። ምክክሩ በዋናነት ዓላማ አድርጎ የተነሳው በሀገራዊ የጋራ ፍላጎቶችና በመሠረታዊ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን በማሳደግ፣ ግጭቶችን ማስቀረትና ሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር ነው። በዚህ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎችም ዘላቂ ሰላምን ያሰፈነች ጠንካራ ሀገርን ለመገንባት የሚያስችል ሐሳብ እንደሚገኝበት ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ መንደል ዓሊ እንደገለፁት፤ በመወያየት የማይፈታ ችግር የለም፤ የአፋር ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓትም ለምክክር ሰፊ ቦታ የሚሰጥ ነው። ምክክሩ በመነጋገር አለመግባባቶችን በጋራ መፍታት እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጠና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት፣ አንድነቷ የጠነከረ ኢትዮጵያን ለመገንባት ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም ምክክሩ የተሻለና ለሀገር አንድነት የሚጠቅም ሐሳብ ይገኝበታል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው፣ ምክክሩ ለኢትዮጵያውያን ብሩህ ተስፋ የሰነቀ መሆኑን ገልጸው ለረጅም ጊዜ መፍትሔ አጥተው ለቆዩ ችግሮችም መፍትሔ እንደሚያመጣ ተስፋ እንዳላቸው አስረድተዋል። ሰላምና ልማትን በላቀ ሁኔታ ለማረጋገጥ ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ሚና እንዳለው የተናገሩት ደግሞ አቶ አስራት ገብረሥላሴ ናቸው። በምክክሩ የቀረቡት አጀንዳዎች የጋራ መገለጫዎቻችንና ሳይፈቱ የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት መንገዱን ያመቻቹ፣ ሰላምና አንድነትን ለማምጣትም ወሳኝ በመሆናቸው በሂደቱ ላይ ተስፋን እንድንሰንቅ አድርጎናል ብለዋል።      
ፖለቲካ
የትግራይ ህዝብ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሚያደርስበትን የግፍና መከራ ለማስቆም ትግሉን ማጠናከር አለበት-የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ
Aug 21, 2026 58
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018(ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል ህዝብ ሕገወጡ የሕወሓት ቡድን በክልሉ እያደረሰበት ያለውን ግፍና መከራ ለማስቆም ትግሉን ማጠናከር እንዳለበት የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ ገለጹ። ቡድኑ ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር የጥፋት ጥምረት በመመስረት ሀገሪቷን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት ከዳረገበት እኩይ ተግባሩ ባለመታቀብ ዛሬም የባዕዳንን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ መሆኑንም ገልጸዋል። የትንሳኤ ሰባ አንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ህገ ወጡ የሕወሃት ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር የጥፋት ጥምረት መመስረት ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት ከዳረገበት እኩይ ተግባሩ የቀጠለ ተልዕኮ የማስፈጸም ሂደት ነው። ሕገ-ወጡ ቡድኑ "ፅምዶ" በሚል ስም ከሻዕቢያ የጥፋት ሀይል ጋር የፈጠረው የጥፋት ጥምረት ኢትዮጵያን ለማፍረስና ከዘላቂ ልማቷ ለማደናቀፍ የተወጠነ የባዕዳን ተልዕኮ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሕገ-ወጥ ቡድን ከምስረታው ጀምሮ የኢትዮጵያዊነት ሥነ-ልቦና የነበራቸውንና ድብቅ አጀንዳውን የተረዱ የትግራይ ተወላጆችን በማጥፋት እና በማስወገድ የፈጸማቸው እኩይ ተግባራቱ ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን አክለዋል። ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በማራቅ ለደህንነት ስጋት እንድትጋለጥ ማድረጉ አስታውሰው፤ ሕገ-ወጥ ቡድኑ ከምስረታው ጀምሮ ለሀገርም ሆነ ለትግራይ ክልል ህዝብ ጥቅም መከበር ከመቆም ይልቅ ለባዕዳን ሀይሎች ተልዕኮ መገዛቱን ያሳያል ብለዋል። ይህ ሕገ-ወጥ የሕወሃት የጥፋት ቡድን ለሰሜኑ ጦርነት መቀስቀስ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚያም በኋላ የፕሪቶሪያውን ስምምነት መጣሱና የጥፋት መንገድ መከተሉ የህገ ወጥ ቡድኑን ለባዕዳን የመላላክ ተፈጥሯዊ ባህሪው መሆኑን እንደሚያሳዩ ተናግረዋል። ሻዕቢያን ጨምሮ ከሌሎች የጥፋት ቡድኖች ጋር ያልተቀደሰ ጥምረት መመስረቱ ኢትዮጵያ ዘላቂ ልማቷን እንዳታረጋግጥና አሁንም ሀገሪቷን ለማመስ የተዘረጋ የባዕዳን ፕሮጀክት አካል መሆኑንም አመልክተዋል። ሕገ-ወጥ የሕወሃት ቡድን የጥፋት ተልዕኮን ለመፈጸም "ፅምዶ" በሚል መጠሪያ ከሻዕቢያ መንግስት ጋር የፈጠረው ጥምረት ኢትዮጵያን ከልማቷ እና ከሰላሟ ወደ ኋላ ለማስቀረት የተወጠነ የባዕዳን ሀይሎች እኩይ ሴራ እንደሆነም ገልጸዋል። የውጭ ኃይሎችን ፍላጎት በትግራይ ክልል ወጣቶች መስዋዕትነት ለማስፈጸም የሚደረገው ጥረት፣ በህዝቡና በወጣቱ ንቃት ምክንያት እንደፈለገው ሊሳካ አለመቻሉን ተናግረዋል። ሕገ-ወጡ ህወሓት የላኪዎቹን ተልዕኮ ለመፈጸም ጥረት የሚያደርግ ቢሆንም፤ የትግራይ ክልል ህዝብ፣ ወጣቱና ምሁራኑ ከቡድኑ ትክክለኛ ማንነት ከየትኛውም ጊዜ በላይ አሁን ላይ መረዳታቸውን ጠቁመዋል። በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የሚኖሩ ትግራይ ክልል ተወላጆች ይበልጥ በመደራጀትና በመተጋገዝ ለቀውሱ ምክንያት የሆነውን አካል በፍጥነት በማስወገድ ረገድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ በውጭ ሀገር የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆችም አስፈላጊውን ተፅዕኖ በማሳደር ቡድኑ እያደረሰ ያለውን ግፍና መከራ ለማስቆም መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሔ ለማበጀት ትልቅ ዕድል የፈጠረው-ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ
Aug 21, 2026 76
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሔ በማበጀት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ተመካካሪዎች ገለጹ። ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወደ ማጠቃለያ ምዕራፍ ደርሷል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ረዳት ፕሮፌሰር አብዱልወኪል ሀሰን ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደገለጹት፥ ምክክሩ የአሳታፊነት መርሆዎችን በጠበቀ መልኩ እየተካሄደ ነው። ለምክክር በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት ያንሸራሸረበት መሆኑን ጠቁመዋል። ለነገዋ የተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ጥሩ ልምድ መሆኑን ተናግረዋል። ምክክሩ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸው፤ ምክክር ለችግሮች መፍቻ ቁልፍ መሆኑን አመልክተዋል። ሌላዋ ተመካካሪ ዓለምፀሐይ ተስፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በምክክሩ በተደረጉ የቡድን ውይይቶች የተለያዩ ሀሳቦች በሚገባ የተንሸራሸሩ መሆኑን ገልጸዋል። "ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት ነው፤ እዚህ የተሰባሰብነውም ዘላቂ ሰላም የመገንባት ሀገራዊ ውጥን ውጤታማ እንዲሆን መሰረት ለማኖር ነው" ብለዋል። ምክክሩ የኢትዮጵያን ቋጠሮዎች ለመፍታት ሁነኛ መንገድ በመሆኑ በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ በመሳተፌም እጅግ ደስተኛ ነኝ ብለዋል። በምክክሩ ላይ ለኢትዮጵያ ይበጃሉ ያልናቸውን ሀሳቦች ሁሉ አቅርበናል ያሉት ደግሞ ሌላው የምክክሩ ተሳታፊ አሳምነው ዋቅጅራ (ዶ/ር) ናቸው። የምክክር መድረኩ ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵያን ያማከለና ሁሉንም አካታች ያደረገ ጥሩ ውይይት የተካሄደበት መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፤ በአጠቃላይ ድምር ውጤቱም ሀገርን የሚያሻግሩ ውጤቶችን እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በመከላከያ እና ደህንነት መስኮች ስትራቴጂካዊ ትብብር ለመመስረት ስምምነት ላይ ደረሱ
Aug 21, 2026 229
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 15 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በመከላከያ እና ደህንነት መስኮች ሁለንተናዊ ስትራቴጂካዊ ትብብር ለመመስረት ስምምነት ላይ ደርሰዋል። የአገር መከላከያ ሚኒስቴር የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ የተመራ ከፍተኛ ወታደራዊ ኃላፊዎችን ያካተተ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በአሜሪካ ከነሐሴ 13 እስከ 14/ 2018 ዓ.ም ጉብኝት በማድረግ በፔንታጎን ከአቻዎቻቸው እና ሌሎች ከፍተኛ የአሜሪካ ጦር ሚኒስቴር አመራሮች ጋር የሁለትዮሽ የጋራ ምክክሮች አድርገዋል። በዚህም በፔንታጎን የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ረዳት የመከላከያ ሚኒስትር ብራያን ጄ. ኤሊስ ጋር በጋራ በተመራ ምክክር የሁለቱን አገራት ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ትብብሮችን ወደ አዲስና የላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ከመግባባት ደርሰዋል። የሁለቱም አገራት የመከላከያ ተቋማት አመራሮች የተቋማቱን ትብብር ለማስፋት እና ስትራቴጂካዊ ቅንጅትን ይበልጥ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ስትራቴጂካዊ ትብብሩ ዘላቂ ብሔራዊ ጥቅምና የጋራ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፣የጋራ መተማመንን በማጠናከር ዘላቂ ትብብር መመስረት እና በአፍሪካ ቀንድ እና በሰፊው ቀጣና ዘላቂ ሰላም፣ ደህንነት እና መረጋጋትን ለማስፈን የጋራ ጥረቶችን ለማሳደግ ዓላማ በሚያደርግ ዋና ዋና ምሰሶዎች የሚመራ ነው። ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ እና ምክትል ረዳት ሚኒስትር ብራያን ጄ. ኤሊስ የተደረሱትን ማዕቀፎች በፍጥነት ወደ ተግባር ለማስገባት እና የሁለትዮሽ የመከላከያ ግንኙነቱን ወደ ተሻለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። በተጨማሪም ልዑካን ቡድኑ በቆይታው ወቅት ከሌሎች የአሜሪካ መከላከያ ተቋማት አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይቶችን ከማድረጉ ባሻገር ጉብኝቶችን ማካሄዱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ ታላቅነት ማሳያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ
Aug 20, 2026 353
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የኢትዮጵያን ታላቅነት ማሳያ ነው ሲሉ ወጣት ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተቃረበ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ወጣት ተመካካሪዎች የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሁሉም ተመካካሪ ድምጽ የተሰማበት እንዲሁም ኢትዮጵያ የራሷን ችግሮች በራሷ እየፈታች ያለችበት ትልቅ መድረክ ነው ብለዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ታረቀኝ በላቸው የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር መሆኗ ማሳያ ነው ሲል ገልጿል። ከሁሉም የማህበረሰቡ ክፍል የተወጣጡ ኢትዮጵያን ለጋራ መግባባት በአንድነት የተሰበሰቡበት መድረክ ነውም ብሏል። በምክክር ሂደቱም የማያግባቡ ነገሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችል ባህል የተገነባበት መሆኑን ነው ያስረዳው። ይህ የምክክር ሂደትም ለአፍሪካ ሀገራት ልምድ መቅሰም የሚችሉበት ነው ሲልም ተናግሯል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ወጣት ገነት መለሰው የምክክር ሂደቱ አካታች በመሆኑ እንደሀገር ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋገጥ እንደሚሆን ያላትን ተስፋ ገልጻለች። ምክክሩ ለሀገረ መንግስት ግንባታ በአንድነት የቆምንበት ነው ያለችው ደግሞ ሌላኛዋ ተመካካሪ ወጣት ፍቲ ሀሠን ነው። ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት በመሰለው መልኩ የሚገልጽበት ሁኔታ እና ለሀገራችን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ በጋራ መግባባት ላይ የደረስንበት ነውም ብላለች። ሌላኛዋ ተመካካሪ መድሃኒት ምትኩ እንደገለጸችው ታሪካዊ እና የመጀመሪያ የሆነው ይህ ምክክር አለመግባባቶችን በምክክር መፍታት እንዳለብን የሚያስገነዝብ መድረክ ነው።    
የአማራ ክልልን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ የጸጥታ ኃይሎች ኃላፊነታቸውን በላቀ ብቃት እየተወጡ ነው
Aug 20, 2026 359
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የአማራ ክልል የሚሊሽያና ሰላም አስከባሪ ሃይሎች የህዝቡን ሰላም በማስጠበቅ ኃላፊነታቸውን በብቃት እየተወጡ መሆኑን የክልሉ ሚሊሽያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ ገለጹ። ኮሚሽነሩ በክልሉ በጽንፈኞች ላይ የሚወሰደውን ህግ የማስከበር እርምጃና አጠቃላይ ሰላም በማስከበር ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም የክልሉ የሚሊሽያ እና ሌሎች የጸጥታ አካላት በቅንጅት የህዝቡን ሰላም በማስከበርና በጽንፈኞች ላይ እርምጃ በመውሰድ ህዝባዊ አደራና ኃላፊነታቸውን በላቀ ብቃት እየተወጡ ይገኛሉ ብለዋል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች በዘረፋ እና እገታ ተግባር ላይ የተሰማሩ ጽንፈኞችን ተከታትሎ እርምጃ የመውሰድ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል። የጽንፈኛ ቡድኑ ዓላማ ከህገ ወጡ ህወሃት እና ሌሎችም ባንዳዎች ጋር በመሆን ታሪካዊ የውጭ ጠላቶችን እኩይ አላማ ማሳካት መሆኑን አንስተው መንግስት ከየትኛውም ጊዜ በላይ ጠንካራ ህግ የማስከበር እርምጃ ይወስዳል ብለዋል። የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች "ጽምዶ" በሚል በመሰባሰብ የህዝብን ሰላም ለማወክ እየጣሩ መሆኑን ያነሱት ኮሚሽነሩ የፀጥታ ሃይላችን ከህዝቡ ጋር በመተባበር ሁሌም ሰላምን ለማስከበር የላቀ ዝግጁነት ላይ ነው ብለዋል። የክልሉን ሰላምና ፀጥታ በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የህዝቡ ድጋፍ፣ ትብብርና እገዛ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
ጉባኤው ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ሀሳብ እንድናዋጣ ዕድል ፈጥሮልናል - ተመካካሪዎች
Aug 20, 2026 360
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ሁላችንም ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ሀሳብ እንድናዋጣ ዕድል ፈጥሮልናል ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ ቆይቶ ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተቃረበ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ተመካካሪዎች መካከል ወጣት መርቀኒያ አሊ፣ ጉባኤው እጅግ ስኬታማ፣ አሳታፊ እና እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት የታየበት መሆኑን ተናግራለች። የምክክር ጉባኤው ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ሃሳብ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ጠቁማ፤ የምክክር ሂደቱ በመደማመጥ ለሀገር ግንባታ ሂደቱ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ የበሰሉ ሀሳቦች የመነጩበት ትልቅ ዕድል ነው ብላለች። መሰል ሀገራዊ የምክክር ሂደት ባህል ሆኖ እንዲቀጥል ከተደረገ የበለጸገችና ታላቅ ሀገር ለመገንባት ጥሩ መደላድል እንደሚፈጥርም ነው የገለጸችው። ይህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ሂደት እስካሁን ለቆዩት ችግሮች የጋራ መፍትሔ ከመስጠት ባለፈ ቀጣዩ ትውልድ ምክክርን ባህል እንዲያደርግ ጠንካራ መሰረት ጥሎ እንደሚያልፍ ተናግራለች። ሌላኛው ተመካካሪ ተረፈ ተከራይ በበኩሉ ሀገራዊ ምክክሩ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ሀሳብ እንድናዋጣ ዕድል ፈጥሮልናል ሲሉ ገልጸዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ቀደም ሲል በሀገሪቱ ለአለመግባባት መንስኤ የነበሩ ጉዳዮችን በጥልቀት ለመመርመር ዕድል የሰጠ ታሪክዊ ጉባኤ ነው ብለዋል። የምክክር ሂደቱ እኩል ሀሳብ የመስጠት ዕድል የተረጋገጠበትና አሳታፊ እንደነበርም ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደፊት የሚያራምዱና ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ግብዓት የሚሆኑ በሳል ሀሳቦች የተንሸራሸሩበት መሆኑን አብራርተዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው መደማመጥ ላይ የተመሰረተ የሀሳብ መዋጮ የተስተናገደበት በመሆኑ ለሀገር ለዘላቂ ሰላምና አንድነት መጠናከር መሰረት የሚጥል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ተመካካሪ ወይዘሮ ሃሊማ ሰይድ ናቸው። ጉባኤው ተመካካሪዎች የአንዱን ችግር እንደራሳቸው እንዲመለከቱ ዕድል በመፍጠር በጋራ የመፍትሔ ሀሳቦች የተመላከቱበት ጉባኤ እንደሆነ ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም የሚያመጣና የጋራ መግባባትን የሚያጎለብት መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል።
የምክክር ጉባኤው ሀገራዊ የምክክር ባህልን በማዳበር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል - ተመካካሪዎች
Aug 20, 2026 432
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የምክክር ባህልን በማዳበር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ ቆይቶ ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተቃረበ ይገኛል። ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ምክክሩ የሀገሪቱን ዘለቂ ሰላም፣ አንድነትና ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ መሠረት የሚጥል ነው። ምክክሩ በልዩነቶች መካከል የጋራ መግባባትን ለመፍጠር እና የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት አዲስ ምዕራፍ መክፈቱንም አስታውቀዋል። ተመካካሪ ካፒቴን ሰለሞን ግዛው እንደገለጹት፣ ምክክሩ የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላምና እድገት በጽኑ መሠረት ላይ ለመጣል የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለችና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ታላቅ ዕድል መሆኑን አስታውቀዋል። በምክክሩ ወቅት የላቀ የመተሳሰብና የሌሎችን ችግር እንደ ራስ የማየት ሂደት መታየቱን የጠቆሙት ካፒቴን ሰለሞን፣ የቡድን አደረጃጀቱም ሀሳብን በነፃነት ለማንሸራሸር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።   ሌላኛዋ ተመካካሪ ወይዘሮ ሰላም ዋቆ በበኩላቸው፣ ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮችን በምክክር መፍትሔ ማበጀት እንደሚቻል በተግባር የተረጋገጠበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። በምክክር ሂደቱ የሁሉም ተሳታፊዎች ሀሳብ ያለ ምንም ልዩነት በእኩልነት የተደመጠበት፣ የጋራ መከባበርና መግባባት የሰፈነበት እንደሆነም አብራርተዋል። ምክክሩ ከሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫዎችና ከውጭ ሀገራት የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጥላ ስር ተሰባስበው ሀገራቸውን ወደተሻለ ደረጃ ለማሻገር የመከሩበት ታሪካዊ መድረክ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሻለቃ ባሻ ተረፈ ወላኒ ናቸው።   የምክክር ሂደቱ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ያሳተፈና አካታች እንደነበር ያነሱት ሻለቃ ባሻ ተረፈ፣ መድረኩ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም፣ ወንድማማችነትና ሀገራዊ አንድነት እንዲጸና ለማድረግ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል። በምክክሩ ወቅት የታየው የመደማመጥና የመመካከር በጎ ልምድ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ሀገራዊ የፖለቲካና የማህበራዊ ባህል ሆኖ በዘላቂነት ሊቀጥል እንደሚገባም ጠቁመዋል።
ምክክሩ ዘላቂ ሰላምን ያሰፈነች ጠንካራ ሀገርን ለመገንባት የሚያስችል ሐሳብ እንደሚገኝበት ተስፋ እናደርጋለን-የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች
Aug 20, 2026 382
ሰመራ፣ነሀሴ 14/2018 (ኢዜአ)፡-ሃገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምን ያሰፈነች ጠንካራ ሀገርን ለመገንባት የሚያስችል ሐሳብ እንደሚገኝበት ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ዘመናትን ያስቆጠሩ ችግሮቻችንን በውይይት ለመፍታት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እየተካሄደ ያለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወደ ማጠቃለያ ምዕራፍ እየተቃረበ ነው። በምክክር መድረኩ ላይ ከመላው የሀገራችን ክፍሎችና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተወካዮችን ጨምሮ አራት ሺህ ተሳታፊዎች የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ በስምንት አጀንዳዎች ላይ በንቃት ሲሳተፉ ቆይተዋል። ምክክሩ በዋናነት ዓላማ አድርጎ የተነሳው በሀገራዊ የጋራ ፍላጎቶችና በመሠረታዊ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን በማሳደግ፣ ግጭቶችን ማስቀረትና ሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር ነው። በዚህ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎችም ዘላቂ ሰላምን ያሰፈነች ጠንካራ ሀገርን ለመገንባት የሚያስችል ሐሳብ እንደሚገኝበት ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ መንደል ዓሊ እንደገለፁት፤ በመወያየት የማይፈታ ችግር የለም፤ የአፋር ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓትም ለምክክር ሰፊ ቦታ የሚሰጥ ነው። ምክክሩ በመነጋገር አለመግባባቶችን በጋራ መፍታት እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጠና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት፣ አንድነቷ የጠነከረ ኢትዮጵያን ለመገንባት ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም ምክክሩ የተሻለና ለሀገር አንድነት የሚጠቅም ሐሳብ ይገኝበታል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው፣ ምክክሩ ለኢትዮጵያውያን ብሩህ ተስፋ የሰነቀ መሆኑን ገልጸው ለረጅም ጊዜ መፍትሔ አጥተው ለቆዩ ችግሮችም መፍትሔ እንደሚያመጣ ተስፋ እንዳላቸው አስረድተዋል። ሰላምና ልማትን በላቀ ሁኔታ ለማረጋገጥ ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ሚና እንዳለው የተናገሩት ደግሞ አቶ አስራት ገብረሥላሴ ናቸው። በምክክሩ የቀረቡት አጀንዳዎች የጋራ መገለጫዎቻችንና ሳይፈቱ የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት መንገዱን ያመቻቹ፣ ሰላምና አንድነትን ለማምጣትም ወሳኝ በመሆናቸው በሂደቱ ላይ ተስፋን እንድንሰንቅ አድርጎናል ብለዋል።      
ማህበራዊ
ኢትዮጵያ በማህበረሰብ አቀፍ እና አማራጭ የፍትሕ ስርዓቶችን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ አብነት የሚሆን ስራ እያከናወነች ነው -በኔዘርላንድስ ሄግ የሚገኘው የሕግ ፈጠራ ተቋም
Aug 21, 2026 64
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አማራጭ ሀገር በቀል የክርክር መፍቻ ስልቶችን ወደ ማህበረሰቡ በማቅረብ የፍትሕ ስርዓቷን ለማሻሻል የምታደርገው ጥረት በአብነት የሚጠቀስ መሆኑን ተቀማጭነቱን በኔዘርላንድስ ሄግ ያደረገው የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) አስታወቀ። የተቋሙ ዋና ኦፕሬቲንግ ኦፊሰር ሼካር ፑላ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥ ኢትዮጵያ የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከላትን (CJCs) ተደራሽነት እያሰፋችበት ያለችበትን መንገድ እና የሀገር ሽማግሌዎችን በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ለማካተት የምታደርገውን ጥረት አድንቀዋል። ይህ አማራጭ የበለጠ ተደራሽ፣ ቀልጣፋ እና ሰላማዊ የፍትሕ ስርዓትን ለመገንባት የሚያስችል ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በማህበረሰባዊ የፍትሕ አማራጭ እና አዳዲስ የፍትሕ መስጫ መንገዶች በእርግጥም ከግንባር ቀደም ሀገራት አንዷ ናት ብለዋል። የፍትሕ ሚኒስቴር ከአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች እና ህዝብን ማዕከል ካደረገ የፍትሕ አሰራር ጋር በተያያዘ ላሳየው ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ አመርቂ ስራ እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ መልካም ተሞክሮዎችን እየቀሰመች ልምዷን ለሌሎች ሀገራት የማካፈል ትልቅ አቅም እንዳላት አንስተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት በሲዳማ ክልል የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከል በተከፈተበት ወቅት ያደረጉትን ጉብኝት በማስታወስ፣ የፍትሕ ስርዓቱ ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር ያለውን አዎንታዊ ግንኙነት አድንቀዋል። በጉብኝታቸው የፍትሕ ሚኒስቴር ለባህላዊ መሪዎች ያለውን አክብሮት ለመመልከት መቻላቸውንና ዘመናትን ያስቆጠሩ የማህበረሰብ አቀፍ የክርክር መፍቻ ልምዶቻቸው ከመደበኛው የፍትሕ ስርዓት ጎን ለጎን እንዴት መስራት እንደሚችሉ መመሪያ መስጠቱን አውስተዋል። ይህ የፍትሕ አማራጭ ትልቅ ተስፋ ያለው፣ ሊሰፋ የሚችል እና ወደፊት ኢትዮጵያን በጥሩ ሁኔታ ሊጠቅም የሚችል አሰራር ነው ብለዋል። መደበኛ ያልሆነ የፍትሕ አሰጣጥ ስርዓት አለመግባባቶችን በፍጥነት ለመፍታት እና የበለጠ ሰላማዊ ማህበረሰብ ለመገንባት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ጠቁመዋል። ይህ አማራጭ ህዝቡ ወደ ዋና ዋና ከተሞች ወይም ወደ ሩቅ ፍርድ ቤቶች ከመጓዝ ይልቅ ባለበት ማህበረሰብ ውስጥ ፍትህን በቅርበት ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል። ለባህላዊ መሪዎች የተዘጋጁ መመሪያዎች የማህበረሰብ እሴቶችን በጠበቀ መልኩ፣ አለመግባባቶችን በመፍታት ረገድ የበለጠ ወጥ እና መረጃን መሰረት ያደረጉ አማራጮችን በማሳደግ ስርዓቱን የበለጠ ሊያጠናክሩት እንደሚችሉ ተናግረዋል። ለኢትዮጵያ የፍትሕ ማሻሻያ ጥረቶች ማዕከል የሆነው እ.አ.አ. በ2019 የተካሄደው የፍትሕ ፍላጎት እና እርካታ ጥናት መሆኑን ጠቅሰው፤ ጥናቱ በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን ለመለየት የረዳ እና ህዝብን ማዕከል ያደረጉ ማሻሻያዎች ላይ አስፈላጊ መሰረት የጣለ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አውስተዋል። ጥናቱ የፍትሕ አገልግሎቶችን በዜጎች እውነተኛ ፍላጎቶች እና ተሞክሮዎች ዙሪያ የመቅረፅን አስፈላጊነት ያሳየ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል። በብዙ ሀገራት እንሰራለን፤ በፍትሕ ሚኒስቴር በኩል ያለው ቁርጠኝነት ግን አርአያነት ያለው ነው ብለዋል። የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት እ.ኤ.አ. በ2019 ከቀድሞው ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመበት ጊዜ አንስቶ የዘለቀ ነው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ተቋሙ በሲዳማ እና አፋር ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በሌሎች አካባቢዎች የመደበኛ ፍትሕ ተቋማትን ማህበረሰብ አቀፍ እና ባህላዊ አሰራሮች ጋር የማስተሳሰር ስራን እንዲሁም የማህበረሰብ ፍትሕ ማዕከላትን ሲደግፍ ቆይቷል። ይህ እንቅስቃሴ ፍትህን ተደራሽ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን፣ በተለይም በቦታ፣ በፋይናንስ ወይም በተቋማት ምክንያት ለመደበኛ ፍርድ ቤቶች ተደራሽ ያልሆኑ ዜጎች ምላሽ ሰጪ ለማድረግ የሚደረገውን ሰፊ ጥረት የሚያንጸባርቅ ነው። የፍትሕ አገልግሎቶችን ወደ ማህበረሰቡ በማቅረብ እና ባህላዊ ተቋማት በግልጽ ማዕቀፍ ውስጥ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበትን እድል በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ የካበቱ የማህበረሰብ ልምዶችን ከዘመናዊ የፍትሕ አማራጮች ጋር ለማዋሃድ እየሰራች ይገኛል። ይህም ኢትዮጵያ የቆዩ ቅሬታዎችን ለመፍታት፣ ማህበራዊ ትስስርን ለማጠናከር እና አለመግባባቶችን ለመፍታት የበለጠ ሰላማዊ የአሰራር ዘዴዎችን ለመገንባት እንዲሁም የሽግግር ፍትሕ ሂደት እና የሀገራዊ የምክክር ስራዎችን እያከናወነች ባለችበት በአሁኑ ወቅት የመጣ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ለሄግ የሕግ ፈጠራ ተቋም (HiiL) የኢትዮጵያ ተሞክሮ ከሀገሪቷ ባሻገር ለሌሎች ሀገራት መልካም ትምህርቶችን የሚሰጥ መሆኑን ኦፊሰሩ ተናግረዋል።
በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው
Aug 21, 2026 74
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018(ኢዜአ) ፦ በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ተግባራዊ መገለጫ መሆኑንም አቶ ጌቱ ተናግረዋል።   የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትና ኢኒሼቲቮችን አፈፃፀም በገመገመበት ወቅት አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት አምጥተዋል። በተለይ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና ተጠቃሚነትን ለሚያረጋግጡ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል። በዚህም የአረጋውያንና አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እድሳትና መልሶ ግንባታ፣ የአካባቢ ንጽህና ጥበቃ፣ ችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ፣ የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠትና የትምህርት ቁሳ ቁስ ድጋፍ የማሰባሰብ ስራዎች መጠናከራቸውን ቀጥለዋል።   የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ማሳያ ነው ያሉት ኃላፊው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በሌላ በኩል አመራሩ ለፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ እና የ 7 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና ልዩ ትኩረት በመስጠት እንዲሰራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በክልሉ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተጀመሩ የቅዳሜ ገበያዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ገልፀዋል።
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ተግባራዊ መገለጫ ነው
Aug 21, 2026 77
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ተግባራዊ መገለጫ መሆኑን የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ። የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትና ኢኒሼቲቮችን አፈፃፀም ገምግሟል። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት፥ በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው። በተለይ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ- ግብር የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና ተጠቃሚነትን ለሚያረጋግጡ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። በዚህም የአረጋውያንና አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እድሳትና መልሶ ግንባታ፣የአካባቢ ንጽህና ጥበቃ፣ ችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ፣ የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠትና የትምህርት ቁሳ ቁስ ድጋፍ የማሰባሰብ ስራዎች መጠናከራቸውን ቀጥለዋል። የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ማሳያ ነው ያሉት ሀላፊው፥ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
በሐረሪ ክልል በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያት የሚከሰቱ አደጋዎችን የመከላከል እና ፈጣን ምላሽ የመስጠት ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Aug 20, 2026 324
ሐረር፤ ነሐሴ 14/ 2018 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያት የሚከሰቱ አደጋዎችን የመከላከል፣ የመቀነስ እና ፈጣን ምላሽ የመስጠት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ። የሐረሪ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር እና ማኅበረሰብ አቀፍ እንክብካቤ ጥምረት ምክር ቤት በክልሉ የሚከሰቱ አደጋዎችን የመከላከል፣ የመቀነስ እና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅምን ለማጠናከር ያለመ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።   ምክር ቤቱ በ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት፣ በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ፣ በቀጣይ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች እና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰፊው ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ለአደጋዎች የማይበገር ማኅበረሰብን ለመገንባት አደጋዎች ከመከሰታቸው በፊት የመከላከልና የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች ልዩ ትኩረት መስጠት ይገባል። የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች የሚያደርሱትን ጉዳት ለመከላከልና ለመቀነስ የማኅበረሰቡንና የባለድርሻ አካላትን የተቀናጀ ጥረት ማጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል። በተለይም በክልሉ ከዝናብ እጥረት ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ ጉዳቶችን ለመከላከልና ሊያጋጥም የሚችለውን የምርት ቅነሳ ለማካካስ የሚያስችሉ የተቀናጁ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። የዝናብ እጥረት ጫና በግብርና፣ በውሃ አቅርቦትና በሌሎች ዘርፎች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር በመሆኑ የተቀናጀ ጥረት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። በራስ አቅም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የመስኖ ልማትን ማጠናከር፣ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የምርት ክምችትን ማጠናከር እና የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ከዝናብ ጥገኝነት ማላቀቅ እንደሚገባም ጠቁመዋል። የክረምቱ ዝናብ ሁኔታ የሰብል እጥረት ሊያስከትል ስለሚችል፣ አርሶ አደሮች የሚገኘውን እርጥበት በአግባቡ የማቆር ሥራዎችን በልዩ ትኩረት ሊያከናውኑ እንደሚገባ መክረዋል። በተጨማሪም እርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህልን ማጠናከር፣ ሁሉንም የሀብት አሰባሰብ አማራጮች መጠቀም እና ድጋፎችን ተቋማዊ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ምርታማነትን የሚጨምሩ አሰራሮችን ከመከተል ባሻገር ድርቅን የሚቋቋሙና በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚደርሱ የሰብል ዝርያዎችን መዝራት፣ ለከብቶች መኖ ማከማቸት እንዲሁም ውሃ ማጠራቀምን የመሰሉ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ተገቢና አስፈላጊ ነው ብለዋል። በውይይቱ የውሃ አጠቃቀምን በማሻሻል፣ የመስኖ ልማትን በማስፋፋት እና ፈጣን የእርሻ ድጋፎችን በማቅረብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። ምክር ቤቱ የሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎችን በራስ አቅም ለማስፈጸም የሚያስችል የበጀት ሰነድ እና የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ የሀብት አሰባሰብ ረቂቅ መመሪያ ላይ በጥልቀት በመወያየት አጽድቋል። የምክር ቤቱ አባላትም በአደጋ ስጋት ቅነሳ እና ምላሽ አሰጣጥ ሂደት ላይ የሚታዩ ማነቆዎችን በመቅረፍ ረገድ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚያበረክቱ ገልጸዋል። አደጋዎች በሚከሰቱበት ወቅት ፈጣን ምላሽ ሰጪ ስርዓት በመዘርጋትና ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር የተቀመጡ የቅድመ ጥንቃቄ ውሳኔዎችን ወደ ተግባር ለመለወጥ ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።
ኢኮኖሚ
ኢትዮጵያ የግብርና ምርቷን ለማሳደግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ነው
Aug 21, 2026 44
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ የግብርና ልማትን ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ በመስኖ ልማት፣ በተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችና በግብርና ሜካናይዜሽን ላይ በትኩረት እየሰራች መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት አምባሳደሮች ኮሚቴና የኢጋድ ፓርላማ ፎረም በአግሪፉድ ሲስተም ዙሪያ በአዲስ አበባ ያዘጋጁት ከፍተኛ የልምድ ልውውጥ መድረክ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የግብርና ልማትን ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ በመስኖ ልማት፣ በተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችና በግብርና ሜካናይዜሽን ላይ በትኩረት እየሰራች ነው። የክላስተር እርሻ ልማት አርሶ አደሮች የግብዓት፣ የቴክኖሎጂ፣ የባለሙያ ምክክር አገልግሎትና የገበያ ትስስሮችን በተሻለ ሁኔታ እንዲያገኙ እያስቻለ መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም በአረንጓዴ ዐሻራ እና በሌማት ትሩፋት ተነሳሽነቶች የአካባቢ ጥበቃን፣ የግብርና ምርታማነትንና የቤተሰብ ምግብና የአመጋገብ ስርዓትን ለማሻሻል ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ተወካይና በድርጅቱ የውጭ አገልግሎት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ኦማር ጃማ የአግሪፉድ ሲስተም ለውጥ የካምፓላ የግብርና ልማት ቃል ኪዳንን ወደ ተግባር በማሸጋገር፣ በጠንካራ ፖሊሲ፣ የሕግ ማዕቀፍ፣ በጀትና ኢንቨስትመንት በመደገፍ እንደሚሳካ ጠቁመዋል። ሀገራቱ ለምግብ ዋስትና ችግር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ፣ ለዝቅተኛ ምርታማነትና ለውስን የገበያ ትስስር የተጋለጡ በመሆኑ፣ የግብርና ለውጥን ለማፋጠን አባል ሀገራት የተቀናጀ ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል። በመድረኩ የአግሪፉድ ሲስተም ልማትን ለማፋጠን የፖሊሲ ቅንጅትን፣ የግብርና ኢንቨስትመንትን፣ የቀጣናዊ ንግድ ትስስርንና የፓርላማ ክትትልን ማጠናከል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
አረንጓዴ አሻራ ከአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ጋር መቀናጀቱ ውጤታማ አድርጎናል-አርሶ አደሮች
Aug 21, 2026 70
ገንዳውሃ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ጋር በማቀናጀት ተጠቃሚ መሆናቸውን የዞኑ አርሶ አደሮች ገለጹ። በዞኑ የቆላ ፍራፍሬ ልማትን በኩታ ገጠም እርሻ ለማልማት ትኩረት ተሰጥቶ እየተከናወነ ይገኛል። በልማቱ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አርሶ አደር ደሴ ባይተኩስ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ጋር አስተሳስረው በመስራታቸው አመርቂ ውጤት አግኝተዋል። በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ያለሙትን ሙዝና ማንጎ ለገበያ በማቅረብ ከ150 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ነው የሚናገሩት። በተለይ "በክላስተር መደራጀታችን የውሃ አጠቃቀማችንን እና የግብዓት አቅርቦት ችግራችንን አቃልሎልናል" ያሉት አርሶ አደሩ፣ በዘንድሮው ዓመትም የተሻለ ምርት ለማግኘት እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ሌላኛዋ የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ፀጋነሽ ብዙነህ በበኩላቸው፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተግባራዊ መደረጉ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በስፋት ለመሳተፍና ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችል ዕድል ይዞ መምጣቱን ገልጸዋል። ሁለት ሄክታር በሚጠጋ መሬት ካለሙት ሙዝ፣ ማንጎና ፓፓያ ከእለት ፍጆታ በተጨማሪ ለገበያ የሚተርፍ ምርት በማምረት ከ100 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፥ በዞኑ በ1 ሺህ 113 ሄክታር መሬት ላይ የቡናና የቆላ ፍራፍሬ ልማት እየተካሄደ ይገኛል። ከዚህ ውስጥ 200 ሄክታሩን በክላስተር በፓፓያና በሙዝ ለማልማት በተጀመረው ስራ እስካሁን ከ40 ሄክታር በላይ መሬት መሸፈኑን ገልጸዋል። የፓፓያና የሙዝ ክላስተር ልማትን ይበልጥ ለማስፋፋት መምሪያው ልዩ ትኩረት መስጠቱን የጠቀሱት ኃላፊው፥ አስፈላጊው ግብዓት በወቅቱ ለአርሶ አደሮች እንዲሰራጭ መደረጉን ተናግረዋል።
የማዕድን ዘርፉን የወጪ ንግድ ከማሳደግ ባለፈ ከውጭ የሚገባውን የኢንዱስትሪ ግብዓት የመተካቱ ስራ ይጠናከራል
Aug 21, 2026 79
ሃዋሳ ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ) ፦ በበጀት ዓመቱ የማዕድን ዘርፉን የወጪ ንግድ ገቢ ከማሳደግ ባለፈ ከውጭ የሚገባውን የኢንዱስትሪ ግብዓት የመተካቱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ። በማዕድን ሚኒስቴር የማዕድን ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ብርሃኔ ያዴሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ከአምስቱ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ከሆነው የማዕድን ዘርፍ ኢትዮጵያ ተገቢውን ጥቅም እንድታገኝ የተከናወኑ የለውጥ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል። ዘርፉ የሚያስገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ በተደረገ ተቋማዊ ሪፎርም የማዕድን መረጃዎችን በዘመናዊ መልክ በማደራጀት መረጃን መሠረት ያደረገ የማዕድን አመራር ሥርዓት ተዘርግቷል ብለዋል። የማዕድን ፍለጋዎችንና ሳይንሳዊ ሥራዎችን ከማጠናከር ባለፈ፣ ማበረታቻዎችንና ምቹ መደላድሎችን በመፍጠር ዘርፉ የኢኮኖሚው ሞተር እንዲሆን የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውንም ገልጸዋል። በመሆኑም በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመትም በሀገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን 5 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር የወጪ ንግድ ገቢ ከማዕድን ማግኘት ተችሏል ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም ከወርቅ በተጨማሪ በተመረጡ የማዕድን ዘርፎች ላይ በማተኮር የዘርፉን የወጪ ንግድ ገቢ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ግብ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። ወርቅ ላይ ብቻ የተንጠለጠለውን የወጪ ንግድ ገቢ ለማስፋት፣ ዓለም አቀፍ ፍላጎትን መሠረት በማድረግ በጌጣጌጥና በሌሎች የተመረጡ ማዕድናት ላይ በማተኮር ገቢን የማሳደግና ዘላቂነትን የማረጋገጥ ሥራዎች ይከናወናሉ ብለዋል። በተኪ ምርት ረገድም ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ከውጭ የሚገቡ ማዕድናትን በሀገር ውስጥ የመተካት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፣ አንዳንድ ተኪ ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ ዕቅድ የተያዘበት ዓመት መሆኑንም ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ሥራ አስኪያጅ አቶ መስፍን መጩካ በበኩላቸው፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የማዕድናት ልየታ ሥራ በትኩረት መከናወኑን ገልጸዋል።   በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 1 ሺህ 350 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መግባቱንና ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ከ11 ሺህ ቶን በላይ ማዕድናት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረባቸውን ተናግረዋል። በኮንስትራክሽን ማዕድናትም የሕብረተሰቡን ፍላጎት የሚያሟሉ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት የሚያስችሉ የማርብልና ግራናይት ማዕድናት ወደ ምርት የማስገባት ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። በክልሉ በጥናት የተለዩ ከ22 በላይ ማዕድናት መኖራቸውን የገለጹት ደግሞ በኤጀንሲው የማዕድን ሀብት ዳይሬክተር ወ/ሮ ምርትነሽ መኮንን ናቸው። ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግም በወርቅ፣ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪ ማዕድናት ላይ የተሰማሩ ከ320 በላይ ማኅበራት የገበያ ትስስር እንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል። በማርብልና ግራናይት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጥቶ ወደ ምርት ለመግባት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር የዓለም ንግድ ድርጅት የሁለትዮሽ ገበያ ዕድል ስምምነት ተፈራረመች
Aug 20, 2026 313
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦​ኢትዮጵያ ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር በዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት ሂደት ማዕቀፍ ስታካሂድ የቆየችውን የሁለትዮሽ የገበያ ዕድል ድርድር በስኬት በማጠናቀቅ የስምምነት ሰነድ ተፈራርማለች። ​የስምምነት ሰነዱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ዋና ተደራዳሪ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች ተፈራርመውታል። ​በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ይህ ታሪካዊ ስምምነት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም እና የፖሊሲ ምህዳር ሙሉ በሙሉ ባስጠበቀ መልኩ የተከናወነ ነው ብለዋል። አክለውም ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት የቆየ ዲፕሎማሲያዊ፣ የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ፣ ኢትዮጵያ በዓለም ንግድ ድርጅት ሙሉ አባል ለመሆን የምታደርገውን ጥረት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ወሳኝ ስኬት መሆኑን አብራርተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች በበኩላቸው፤ የተደረገው ስምምነት የሁለቱን ሀገራት የቆየ የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ ግንኙነት ይበልጥ የሚያጎለብት መሆኑን ገልጸዋል። ዩናይትድ ኪንግደም ኢትዮጵያ ወደ ዓለም ንግድ ድርጅት ለመቀላቀል የምታደርገውን ጥረት እና የምታካሂዳቸውን የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በሙሉ ቁርጠኝነት መደገፏን የምትቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። ​ኢትዮጵያ እስካሁን ባለው ሂደት ከቻይና፣ ሩሲያ፣ አርጀንቲና፣ ቱርክ፣ ብራዚል፣ ጃፓን፣ ሕንድ፣ ኒውዚላንድ እና ታይላንድ ጋር ተመሳሳይ ስምምነቶችን ተፈራርማለች። ዩናይትድ ኪንግደም ስምምነቱን በይፋ ከፈረሙ አባል ሀገራት 10ኛዋ እና ድርድሩን በስኬት ካጠናቀቁት ደግሞ 11ኛዋ አባል ሀገር ሆናለች።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስርዓት የባለስልጣኑን የአገልግሎት አሰጣጥ አቀላጥፏል
Aug 20, 2026 138
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በመቀናጀት ተግባራዊ እያደረገ የሚገኘው የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ማስቻሉን የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ጌታቸው (ዶ/ር) ገለጹ። ይህ የተቀናጀ የአንድ መስኮት አገልግሎት አሰጣጥ የተገልጋዮችን እርካታ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ተናግረዋል። መንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ቀልጣፋና ግልጽ አገልግሎት ለመስጠት ዲጂታል 2025 ስትራቴጂን በውጤታማነት በመተግበር ሀገሪቱ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂን ነድፋ እየተገበረች ትገኛለች። በዚህ መነሻ እየተተገበረ ያለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተበታተኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከልና በተቀናጀ አግባብ እንዲመሩ በማድረግ የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ ይገኛል። የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ጌታቸው (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በመቀናጀት ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ቴክኖሎጂዎች ቁጥጥር አገልግሎትን በአንድ መስኮት እየሰጠ ይገኛል። ይህ አሰራር አገልግሎት አሰጣጡን በማቀላጠፍ የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ መሆኑን ገልጸው፤ ይህን የበለጠ ለማላቅ አገልግሎቶቹን በቴክኖሎጂ የማስደገፉን ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በዚህም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ውስጥ የሚገቡ 48 አገልግሎቶች መለየታቸውንና በሂደቱ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። እነዚህ አገልግሎቶች የባለስልጣኑን የአገልግሎት ተደራሽነት ከማስፋት ባሻገር ጥራትና ቅልጥፍናን በማሳደግ የተገልጋዮችን እርካታ የበለጠ እንደሚያሳድጉም አክለዋል። ባለስልጣኑ አሁን ላይ ከዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ባገኘው ቴክኖሎጂ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ቴክኖሎጂዎች ላይ ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የህግ መተላለፎች ሲከሰቱ ምዝገባ፣ ትንተና እና ሌሎች ተገልጋይ ተኮር ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂው ባለስልጣኑ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ግልጽ እና ቀልጣፋ በማድረግ የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ እንደሚገኝ ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ይህን የተገልጋዮች የአገልግሎት እርካታ የበለጠ ለማሳደግ አገልግሎቶቹን ወደ መሶብ የአንድ ማዕከል ማስገባት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ጨምረው ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን
Aug 20, 2026 174
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር በጋራ እንደሚሰሩ በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን ገለጹ። አምባሳደሩ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል።   በጉብኝታቸው ወቅትም አምባሳደሩ አንደተናገሩት በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነት አለ። ይሄንን ግንኙነት መሰረት በማድረግም ሁለቱ ሀገራት በምርምር ፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ይህ የሁለቱ ሀገራት አጋርነት የብሪክስ አባል ሀገራት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ለጋራ ዕድገትና ተጠቃሚነት ለማዋል ከሚያደርጉት ሰፊ ጥረት ጋር የሚጣጣም መሆኑም ተገልጿል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ በሀገሪቱ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ውስጥ እያከናወናቸው ያሉ ወሳኝ ስራዎችን አስመልክተው ለአምባሳደሩ ገለጻ አድርገዋል።   በዚህም ኢንስቲትዩቱ የሚያከናውናቸው የምርምርና የልማት ስራዎች በኢትዮጵያ ቅድሚያ በተሰጣቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ ከፍተኛ እምርታ እንዲመዘገብ ማስቻላቸውን ተናግረዋል፡፡
ዲጂታል 2030፦የኢትዮጵያ አዲሱ የቴክኖሎጂ ዘመን!
Aug 20, 2026 175
የዲጂታል 2025 መጠናቀቁን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ታኅሣሥ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። ይህ አዲስ ምዕራፍ ሀገሪቱ ባለፉት አምስት ዓመታት በዲጂታል ዘርፉ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች አጠናክሮ ለመቀጠል የተዘጋጀ ታላቅ አገራዊ እቅድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች ሲሉ ገልጸዋል።ተደራሽነትን ማስፋት፣እኩል እድል መፍጠር እና በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት የስትራቴጂው ቁልፍ ትልሞች ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ በዓለም ሁለተኛውና ለአፍሪካ የመጀመሪያው የሚሆነውን የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዩኒቨርሲቲ ግንባታ በይፋ አስጀምራለች። ይህ ዩኒቨርሲቲ ሀገሪቱን በዘርፉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግና የላቀ የኤአይ ባለሙያዎችንና ተመራማሪዎችን የሚያፈራ ታሪካዊ ተቋም ይሆናል። ይህ ታላቅ የትምህርት ተቋም ከሀገር ውስጥ አልፎ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል (Scholarship) በማመቻቸት፣ ኢትዮጵያን የአህጉሪቱ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) የማድረግ ራዕይን በግንባር ቀደምትነት የሚያስፈጽም ይሆናል። በቅርቡ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አጋርነት የተመረቀው 'AI UniPod' ማዕከል፣ ወጣቶች በሮቦቲክስ፣ በዳታ ሳይንስና በኤአይ ምርምሮች ላይ እንዲሰማሩ ትልቅ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ፈጥሯል። አዲሱ ስትራቴጂ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠርን ያለመ ነው። ይህም ቢሮክራሲን በመቀነስ ለዜጎች ፈጣንና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል። በተጨማሪም በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና የወጣቶችን የፈጠራ አቅም ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም መቀየር የስትራቴጂው ዋና ግብ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚው ሲያድግ የመረጃ ደህንነት ወሳኝ በመሆኑ፣ የሳይበር ደህንነት መሠረተ ልማቶችን ማጠናከር የዚሁ ዕቅድ ዋነኛ አካል ተደርጎ ተይዟል። ይህም የዜጎችንና የተቋማትን የመረጃ ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የሚያስችል አቅም ይፈጥራል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ተጠቁሟል። ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ በጥራት እንዲያሻሽልና አገልግሎቶችን እንዲያቀልጥ ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በተጨማሪም ይፋ በተደረጉ አገራዊ መረጃዎች መሰረት፣ የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ደንበኞችን ቁጥር 128 ሚሊዮን ማድረስ እና የ5G አውታረ መረብ ተደራሽነትን 100% ማድረስን አልሟል።ይህም የመገናኛ አቅምን በማሳደግ የዲጂታል ክፍተቱን በከፍተኛ ደረጃ ያጠበዋል ተብሎ ይጠበቃል። በሌላ በኩል የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ ማካሄድ ሌላው ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት የሚሰራበት ሀገራዊ ግብ ነው። ይህም አሰራርን ግልጽ፣ ቀልጣፋና ከሙስና የጸዳ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግሥት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ ናቸው። ለዚህም ስኬት የሁሉም አካላት ትብብርና ቅንጅት ወሳኝ መሆኑ ተጠቅሷል። በመጨረሻም፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ስኬት ኢትዮጵያን በቴክኖሎጂ የበለጸገች፣ የወጣቶችን ፈጠራ የምታበረታታ እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ የሚያገለግል ታላቅ የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ነው።    
የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ ነው
Aug 19, 2026 285
ወላይታ ሶዶ ፤ ነሐሴ 13/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አስቴር ዳዊት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ ትግበራ በስኬትና በውጤታማነት ተጠናክሮ መቀጠሉ ይታወቃል።   የዲጂታል መሠረተ ልማቶች መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሳይበር ጥቃቶችን የመከላከልና የሳይበር ሉዓላዊነትን የማስከበር ተግባርም በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል። ይህንኑ ተግባራዊ ጥረት ለማጠናከርም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ከተለያዩ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የወጣቶችን የሳይበር ደህንነት ክህሎት የሚያሳድጉ የክረምት ስልጠና ፕሮግራሞችን በማካሄድ ላይ ይገኛል።   በተለይም የክረምት የስልጠና መርሃ-ግብር በሳይበር ደህንነት፣ በሶፍትዌር ልማት፣ በኮዲንግ እና በመረጃ ደህንነት ዙሪያ የተሻለ ክህሎት ያላቸውን ታዳጊና ወጣቶች በመሰልጠን ላይ ናቸው። በዚሁ መሰረትም የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በክረምቱ በአምስተኛ ዙር በርካታ ወጣቶችን የሳይበር ደህንነት ስልጠና በመስጠት ላይ ሲሆን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አስቴር ዳዊትና ሌሎች የመንግስት ስራ ኃላፊዎች በስፍራው በመገኘት ሰልጣኞችን አበረታትተዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የወጣቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን አንስተው በዚሁ መሰረትም የስልጠና እና ግንዛቤ ስራዎች መቀጠላቸውን ገልጸዋል። በክረምቱ ወላይታ ሶዶን ጨምሮ በስድስት ዩኒቨርሲቲዎች ለወጣቶች ተመሳሳይ ስልጠና በመሰጠት ላይ መሆኑን አንስተው ይህም ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም የሚሆን ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን አንስተው ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል።   የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳይ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት አክበር ጩፎ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ብቁ ዜጎችን የማፍራት ስራውን መቀጠሉን ገልጸዋል። ከቴክኖሎጂ፣ ከኢንዳስትሪና መሰል ተቋማት ጋር የመስራት ዕድል መፈጠሩን ጠቁመው ይህም የተለየ ተሰጥኦ ላላቸው ተማሪዎች መልካም እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።   ከሰልጣኞቹ መካከል ከዲላ ከተማ የመጣችው የ12ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው መልካም አስራት እና ከሐዋሳ ከተማ የመጣችው የ11ኛ ክፍል ተማሪ ኖሐሚን ንጋቱ፤ በስልጠናው ስለ የሳይበር ደህንነትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ መሰረታዊ ዕውቀት በመገብየት በዲጂታሉ ዓለም የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረን አድርጎናል ብለዋል። የወላይታ ሶዶ ነዋሪና በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ ዓመት ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ፍሬው ቶማስ በበኩሉ ይህ ስልጠና ክህሎታቸውን ለማሳደግ አማራጭ ላጡ ወጣቶችና ተማሪዎች መልካም ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል።   በስልጠናው የሳይበር ደህንነት እውቀት ማግኘቱን የጠቀሰው ወጣቱ የመረጃ መንታፊዎችን በመዋጋት የሀገራችንን የመረጃ ደህንነት ለማረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ አረጋግጧል ።
ስፖርት
የተወዳጁ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲስ የውድድር ዘመን በሻምፒዮኑ አርሰናል እና ኮቨንተሪ ሲቲ ጨዋታ ይጀመራል
Aug 21, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ጅማሮውን ያደርጋል። ምሽት አራት ሰዓት ላይ አርሰናል ከኮቨንተሪ ሲቲ ጋር በኤምሬትስ ስታዲየም ጨዋታውን ያደርጋል። አርሰናል የወቅቱ የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ነው። ተጋጣሚው ኮቨንተሪ ሲቲ ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ተመልሷል። ሁለቱ ቡድኖች በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሲገናኙ የአሁኑ ለ19ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 18 ጨዋታዎች አርሰናል 10ሩን በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ኮቨንተሪ ሲቲ ሦስት ጊዜ ሲያሸንፍ በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። አርሰናል በ18ቱ ጨዋታዎች ላይ 25 ጎሎችን ሲያስቆጥር ኮቨንተሪ ሲቲ 13 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሁለቱ ቡድኖች ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ የተገናኙት እ.አ.አ በ2001 ነበር። በወቅቱ ባደረጉት ጨዋታ አርሰናል በዴኒስ ቤርካምፕ ጎል 1 ለ 0 አሸንፏል። ኮቨንተሪ ሲቲ በዛው ዓመት ከሊጉ ወርዷል። ኮቨንተሪ በፍራንክ ላምፓርድ እየተመራ በሻምፒዮንሺፑ በ95 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ተመልሷል። በማይክል አርቴታ የሚመራው አርሰናል የሻምፒዮንነት ክብሩን የማስጠበቅ ጉዞውን ከአዲስ አዳጊው ክለብ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ይጀምራል። ኮቨንተሪ ሲቲ በመጀመሪያው የሊግ ጨዋታው ከሊጉ የወቅቱ የዋንጫ ባለቤት ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል። የ36 ዓመቱ ቶም ብራሞል የመክፈቻውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመራሉ። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ለአህጉራዊ ውድድሮች ብቁ መሆኑ ከስፖርቱ ባለፈ ለቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው
Aug 20, 2026 184
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ለአህጉራዊ ውድድሮች ብቁ መሆኑ ከስፖርት ባለፈ ለቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየምን ለአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ዝግጁ ለማድረግ ሰፊ የማሻሻያና የመልሶ ግንባታ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸው ይታወቃል። የስታዲየሙን ለጨዋታ ዝግጁ መሆን ከውድድር ባለፈ በተለይም ለቱሪዝም ያለውን ፋይዳ በተመለከተ የአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አየለ አናውጤ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ለአህጉራዊ ውድድሮች ብቁ መሆኑ ከስፖርትም ባለፈ ለቱሪዝም ዘርፍ ማንሰራራት ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን አስረድተዋል። ከእግር ኳስ ውጭም በከተማዋ የውሃ ዋና፣ የአትሌቲክስ እና የብስክሌት ውድድሮችን ለማስፋት ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ነው የጠቆሙት ። በከተማዋ የተገነቡ እና በመገንባት ላይ ያሉ ባለ ኮከብ ሆቴሎች መኖራቸው የካፍ ባለሙያዎችን መስፈርት የሚያሟላ እና ለዘርፉ ዘላቂ እድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የስታዲየሙ ዝግጁነት ለሀገራዊ የስፖርት እድገት እንዲሁም ለስፖርት ቤተሰቡ እና ለብሔራዊ ቡድኑ ጭምር ትልቅ የምስራች መሆኑን ጠቅሰው ለቱሪዝም ዘርፉም ትልቅ አቅም ይሆናል ብለዋል። ስታዲየሙ የጨዋታ መስፈርቱን አሟልቶና ብቁ ሆኖ መገኘቱ ብሔራዊ ቡድኑ እና ክለቦች አህጉራዊ ጨዋታዎችን በሜዳቸውና በደጋፊዎቻቸው ፊት የመጫወት ዕድል አመቻችቷል።
ካሜሮን ለመጀመሪያ ጊዜ የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫን አነሳች
Aug 17, 2026 322
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በ14ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ካሜሮን ማላዊን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በሞሮኮ ራባት በሚገኘው የሙላይ አል ሀሰን ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ካሜሮን ፍጹም የበላይነትን ወስዳለች። ማሪ ንጋህ በ20ኛው እና በ45ኛው ደቂቃ ላይ ሁለት ግቦችን ከመረብ ስታሳርፍ፣ ናኦሚ ንጆአ ኤቶ በ30ኛው ደቂቃ ላይ ሶስተኛዋን ግብ አክላለች። ማላዊ በሁለተኛው አጋማሽ ጥሩ እንቅስቃሴ ብታደርግም የካሜሩንን የተከላካይ ክፍል ሰብራ ግብ ማስቆጠር አልቻለችም። ካሜሮን ውጤቱን ተከትሎ የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫን ለመጀመሪያ ጊዜ አንስታለች። የማይበገሩት አንበሶች ከዚህ ቀደም ሶስት ጊዜ ለፍጻሜ ደርሰው ማሸነፍ አልቻሉም ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ ለፍጻሜ የቀረበችው ማላዊ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ይህ ድል ለካሜሩን የዋንጫ ክብር ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማትንም ያስገኘ ነው። አሸናፊዋ ካሜሩን ከአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሁለት ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ ሽልማት የምታገኝ ሲሆን፣ ይህ ስኬት ቡድኑን በቀጥታ እ.አ.አ በ2027 በብራዚል ለሚካሄደው 10ኛው የፊፋ የሴቶች የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን ያረጋገጠላት ሆኗል። ከካሜሩን በተጨማሪ ግማሽ ፍጻሜ የደረሱት ማላዊ፣ ሞሮኮ እና ናይጄሪያም አፍሪካን ወክለው በዚህ ታሪካዊ የዓለም ዋንጫ ላይ ይሳተፋሉ። ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው ማላዊ የ750 ሺህ ዶላር ሽልማት ይበረከትላታል። አዘጋጇን ሞሮኮን በደረጃ ጨዋታ በመለያ ምት በመርታት ሶስተኛ የወጣችው አልጄሪያ የ550 ሺህ ዶላር ሽልማት ታገኛለች። ሞሮኮ የ300 ሺህ ዶላር ሽልማት ወደ ካዝናዋ ታስገባለች። ሞኒክ ንጎክ (ካሜሩን) የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች በመባል ተመር ጣለች። ሚካኤሊ ቢሂና (ካሜሩን) በውድድሩ ላይ ባሳየችው ብቃት ኮከብ ግብ ጠባቂ ሆናለች። ቴምዋ ቻዊንጋ (ማላዊ) አምስት ግቦችን በማስቆጠር የኮከብ ግብ አግቢነቱን የወርቅ ጫማ ወስዳለች። ከሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሞሮኮ በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ 12 ሀገራት ተሳትፈውበታል።
በሀዋሳ ከተማ በኮሪደር ልማት የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታን ፈጥረዋል--ከንቲባ ጥራቱ በየነ
Aug 16, 2026 401
ሀዋሳ፤ ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- በሀዋሳ ከተማ በኮሪደር ልማት የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎቸ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታን መፍጠራቸውን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ። “ኮሪደር ልማት ለስፖርት ቱሪዝም” በሚል መሪ ሀሳብ የታዳጊዎችና ወጣቶች የፕሮጀክት ስፖርታዊ ውድድር በሀዋሳ ከተማ ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ እንዳሉት፣ ወጣቶችና ሕጻናት በስፖርቱ ዘርፍ በንቃት እንዲሳተፉ በማድረግ የነገ ተተኪ ስፖርተኞች እንዲሆኑ ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።   በከተማዋ የሚካሄዱ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ወጣቶችን፣ ሕጻናትንና አረጋውያንን ታሳቢ ያደረጉ ምቹ የመዝናኛ፣ የማረፊያና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ያካተቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በስፖርቱ ዘርፍ ሀዋሳ ከተማን፣ የሲዳማ ክልልንና ሀገርን የሚወክሉ ስፖርተኞችን ለማፍራት በአራት ዙር በተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች 15 የሕጻናት መጫወቻ፣ የወጣቶችና ታዳጊዎች ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታዎች በዕቅድ መካተታቸውን አብራርተዋል። ከነዚህም ሦስት የታዳጊዎችና ሦስት የወጣቶች (በጠቅላላው ስድስት) ሰው ሰራሽ ሣር የተነጠፈላቸው የእግር ኳስ ሜዳዎች፣ 4 የቅርጫት ኳስ ሜዳዎች፣ 5 የሕጻናት መጫወቻ ስፍራዎችና የሜዳ ቴኒስ ማዘውተሪያዎች መገንባታቸውን ገልጸዋል። እነዚህም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታን መፍጠራቸውን አመልክተዋል።   አቶ ጥራቱ አክለውም፤ ወጣቶች የእረፍት ጊዜያቸውን በአልባሌ ስፍራ ከማሳለፍ በመራቅ በስፖርት ላይ እንዲያተኩሩና እነዚህን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በአግባቡና በጥንቃቄ እንዲይዟቸው አሳስበዋል። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ በላይነሽ ገዳ በበኩላቸው፣ በከተማዋ በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ለአምስት ቀናት የሚቆይና በእግር ኳስ፣ በቅርጫት ኳስ፣ በብስክሌትና በሜዳ ቴኒስ በሁለቱም ጾታዎች 34 ቡድኖች የሚሳተፉበት የፕሮጀክቶች ስፖርታዊ ውድድር መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የተገነቡት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ለክልሉ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራትና ለዘርፉ መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ የገለፁት ደግሞ የሲዳማ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዶማርሶ ዶና ናቸው። በፕሮጀክት ውድድሩ ላይ ተሳታፊ ከሆኑ ስፖርተኞች መካከል ወጣት ፍላጎት ተሻ እና ወጣት ሚካኤል ፍጹም እንደገለጹት፣ በከተማዋ የተገነቡት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ባላቸው ፍላጎትና ተሰጥኦ መሠረት እንዲሳተፉ አስችሏቸዋል። በክረምቱ ወቅት በተለያዩ መስኮች በፕሮጀክት ታቅፈው ሲሰለጥኑ መቆየታቸው ጊዜያቸውን አልባሌ ቦታ ላይ እንዳያባክኑ ትልቅ እድል እንደፈጠረላቸውም አክለዋል። በስነ-ሥርዓቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩና የክልሉ አመራሮች እንዲሁም ወጣቶች ተገኝተዋል።  
አካባቢ ጥበቃ
በኦሮሚያ ክልል ተመናምኖ የነበረው የደን ሽፋን በአረንጓዴ አሻራ አማካኝነት በፍጥነት እያደገ ነው
Aug 21, 2026 69
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተከናወኑ ተግባራት አማካኝነት ተመናምኖ የነበረው የደን ሽፋን መልሶ እድገት እያሳየ መሆኑን የክልሉ ደን እና ዱር እንስሳት ድርጅት አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል ሰፊ የተፈጥሮ ሀብትና ብዝሃ-ሕይወት ባለቤት ቢሆንም፣ ባለፉት አሥርተ ዓመታት በሕገ-ወጥ የደን ምንጣሮ፣ ለእንጨትና ከሰል ምርት በሚደረግ ጭፍጨፋ እና ለእርሻ መሬት ማስፋፊያ ምክንያት የደን ሽፋኑ በከፍተኛ ደረጃ ተመናምኖ ቆይቷል። ይህ የደን ውድመት አካባቢውን ለአፈር መሸርሸር፣ ለወንዞችና ሐይቆች መድረቅ እንዲሁም ለምርታማነት መቀነስ ዳርጎት የነበረ ሲሆን፣ በተለይም እንደ ሐረማያ ባሉ አካባቢዎች የነበሩ የውሃ አካላት ሙሉ በሙሉ እስከመድ ረቅ ደርሰው የነበረው አካባቢያዊ ሥነ-ምህዳሩ ለከፍተኛ አደጋ ተጋልጦ ስለነበር ነው። ይህንን ሥነ-ምህዳራዊና ምጣኔ-ሀብታዊ አደጋ ለመቀልበስ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢኒሼቲቭ በሀገር ደረጃ እየተካሄደ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉም በየዓመቱ እንደ ዋነኛ መፍትሔ ተወስዶ ሰፊ የተቀናጀ ንቅናቄ በማካሄድ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ውጤት እየመጣ ነው። የኦሮሚያ ክልል ደን እና ዱር እንስሳት ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ አራርሳ ረጋሳ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በክልሉ ባለፉት ዓመታት የደን ሽፋኑን ለማሳደግ የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል። በክልሉ የደን ሽፋኑን ለማሳደግ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል፣ በተለይም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተራቁተው በነበሩ ቦታዎች ላይ ሳይንሳዊ መንገድን በተከተለ መልኩ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ጎን ለጎን አካባቢዎችን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ እንዲሁም ሕገ-ወጥ የእርሻ መሬት ማስፋፋትን ለመግታት በተሠራው ሥራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። በተለይም ችግኞችን በመትከል ላይ ብቻ ሳይወሰን ለእንክብካቤያቸው ከፍተኛ ትኩረት በመሰጠቱ ለውጤቱ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም በክልሉ ከዚህ በፊት ተመናምኖ የነበረው የደን ሽፋን ወደ 27 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ይህ የተቀናጀ ጥረት የአፈር መንሸራሸርን መከላከል፣ የአፈር ለምነትን መመለስ እንዲሁም የደረቁ ምንጮች፣ ሀይቆችና ወንዞች እንደገና እንዲጎለብቱ ያደረገ ሲሆን፣ በዚህም በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ደርቆ የነበረው የሐረማያ ሀይቅ ሙሉ በሙሉ ማገገሙን ለአብነት አንስተዋል። በአጠቃላይ የመርሃ ግብሩ ስኬት በሁሉም ወቅቶች መሬትን በማልማት፣ የአካባቢ ጥበቃን ከግብርና ስራዎች ጋር በማጣመር የምርትና ምርታማነት እድገትን ከማሳደግ አንጻር ከፍተኛ ድርሻ እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል። አቶ አራርሳ እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት በክልሉ በአጠቃላይ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በደን መልማቱን ገልጸዋል። ከአጠቃላይ መሬቱ ውስጥ 1 ሚሊዮን ሄክታር ያህሉ ለዱር እንስሳት እንክብካቤና ጥበቃ፣ ለፓርኮች፣ ለስፖርት ስፍራዎች ሲሆኑ፣ 700 ሺህ ሄክታር መሬት ደግሞ ለችግኝ ተከላ እና ለሰው ሰራሽ ደን ልማት የተመደበ ስፍራ ነው። ከአጠቃላይ መሬቱ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ደግሞ ሙሉ በሙሉ በተፈጥሮ ደን የተሸፈነ መሆኑን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት ኖርዌይ ትደግፋለች
Aug 19, 2026 423
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2018 (ኢዜአ)፦ ኖርዌይ ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትደግፍ በኢትዮጵያ የኖርዌይ ኤምባሲ የደንና አየር ንብረት ጉዳዮች ልዩ መልዕክተኛና አማካሪ ላይቭ ጃኮብ ሲድነስ ገለጹ። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ስጋት የሆነውን የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ለመከላከል በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ በአረንጓዴ ልማትና በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ለቀጣናው ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ተግባር በማከናወን ላይ ትገኛለች። በኢትዮጵያ የኖርዌይ ኤምባሲ የደንና አየር ንብረት ጉዳዮች ልዩ መልዕክተኛና አማካሪ ላይቭ ጃኮብ ሲድነስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በደን ልማት ዘርፍ አስደናቂ ለውጥ ተገኝቷል፡፡   በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርና በአፈርና ውሃ ጥበቃ በተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በሀገሪቱ የደን ሽፋን ላይ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ ኖርዌይ ባለፉት አስርት ዓመታት ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የደን ሽፋን ማሳደግ የሚያስችል እንቅስቃሴ አድርገናል ብለዋል፡፡ የደን ልማት የአፈር መሸርሸርን መከላከልና የአፈርና ውሃ ሀብት ጥበቃ በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንደሚያሳድግ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የደን ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ በቀጣናው የውኃ አቅርቦትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እገዛ እንደሚያደርግም ተናግረዋል፡፡ ኖርዌይ ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የምታከናውነውን ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትደግፍም ገልጸዋል። ሁለቱ ሀገራት በደን ጥበቃ ስራዎች በመተባበር የደን ጭፍጨፋን ለመቀነስ እንደሚሰሩ ጠቅሰው፤ ኖርዌይ የኢትዮጵያ የሬድ ፕላስ መርሃ ግብር ትግበራ ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኗን ተናግረዋል።   በኢትዮጵያ የተነደፈውን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የሚቋቋም አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ለመደገፍ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥልም ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ዘመናዊ የከተሜነት የሥነ-ምኅዳር ከባቢ አጎናፅፏታል
Aug 18, 2026 388
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ውጤታማነት ዘመናዊ የከተሜነት የሥነ-ምኅዳር ከባቢ እንዳጎናጸፋት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ገለጸ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ እየተካሄዱ ያሉትን የኮሪደር፣ የወንዞችና የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን አስመልክቶ ከአካባቢ ጥናት አማካሪ ድርጅቶች ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ እሸቱ ለማ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ የልማት ፕሮጀክቶች ከአካባቢና ከማህበረሰብ ደህንነት ጋር ተጣጥመው እንዲሄዱ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ (EIA) እና ኦዲት ጥናቶች ወሳኝ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተቋማቸው ደረጃውን የጠበቀና ተወዳዳሪ ለመሆን የሪፎርም ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ከአማካሪ ድርጅቶች የሚገኙ ግብዓቶች ተቋማዊ አሰራሩን ለማዘመንና የታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት እንደሚረዱም ነው የገለጹት። በባለሥልጣኑ የአካባቢና ማህበረሰብ ተፅዕኖ ግምገማ ቡድን መሪ አቶ አብዲ ቀሊ በበኩላቸው፤ አማካሪ ድርጅቶች የሚያቀርቧቸው የጥናት ሰነዶች በጥራትና በሳይንሳዊ ደረጃቸው ብቁ ሊሆኑ እንደሚገባ አስረድተዋል። የመድረኩ ዋና ዓላማ የብክለት መጠንን በጥናት በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫ ማስቀመጥ መሆኑም ተጠቁሟል።
በፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር ቅንጅታዊ ሥራዎች ቀጥለዋል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Aug 17, 2026 198
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ) ፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማና አምራች ዜጋን በመፍጠር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ ሥራዎች መቀጠላቸውን የክልሉ ርዕሰመስተዳደር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ። "ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" በሚል መሪ ሀሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ ለ3ኛ ዙር የተዘጋጀ የፅዱ ኢትዮጵያ የንቅናቄና የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል። ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ እንዳሉት በክልሉ በፅዱ ኢትዮጵያ ጤናማና አምራች ዜጋን በመፍጠር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ ሥራዎች ቀጥለዋል። ንቅናቄው ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር እያገዘ እንደሚገኝ ገልጸው፣ በቀጣይም ህዝቡን ባለቤት በማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ይሰራል ብለዋል። ለዚህም ጽዳትን ባህሉ ያደረጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አመልክተዋል። የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ የአመራሩንና የባለድርሻ አካላትን ርብርብ ወሳኝ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በበኩላቸው እንዳሉት በመደመር መንግስት እሳቤ የአካባቢ ጥበቃ ሥራን በጋራ በማከናወን ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል።   የጽዱ ኢትዮጵያ ቀጣይ 3 ወራት ንቅናቄም ፕላስቲክን በአግባቡ የመጠቀም፣ የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው የፋብሪካ ኬሚካሎች አወጋገድና የድምጽ ብክለትን መከላከል ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል። የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ለተተኪው ትውልድ ጤናማና ምቹ አካባቢን ለማስተላለፍ የሚከናወኑ ተግባራት እንደሚጠናከሩም አክለዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደን አካባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ አብርሃም መጫ እንደገለጹት በክልሉ የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ትግበራ የተራቆተ መሬትን በማልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አስችሏል።   ከዚህ በተጨማሪ የከተሞችን ውበት ማስጠበቅን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ውጤቶች እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል። ቢሮው በቀጣይ 3 ወራት በሚተገበረው የፅዱ ኢትዮጵያ ኢንሼቲቭ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።   በመድረኩ የክልሉ፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እና ተጋባዥ እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 930
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 843
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 1123
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1671
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
ቡሄ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ምስረታ ታሪካዊ ቁርኝት
Aug 19, 2026 289
በሙሴ መለሰ ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን የቡሄ በዓል በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ባለበት በዚህ ዕለት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አጀማመሩንና ምስረታውን ከዚህ በዓል ጋር ያለውን የጠበቀ ትስስር ወደ ኋላ መለስ ብሎ የሚታወስበት ነው። የክለቡ ምስረታና የቡሄ በዓል (የሆያ ሆዬ ጨዋታ) ቀጥተኛና የማይነጠል ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፣ ክለቡ በመስረታው ወቅት የነበረበትን የፋይናንስ እጥረት ቀርፎ የመጀመሪያውን ማሊያ ለመግዛት የበቃው በዚህ ዕለት በተሰበሰበ የሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ነበር። የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን መጀመሪያ ሲጠነሰስ በጆርጅ ዱካስና በአየለ አትናሽ አማካኝነት የነበረ ቢሆንም፣ ክለቡን በይፋ አደራጅቶ ለማቋቋም ግን የግድ የፋይናንስ አቅም ወይም ገንዘብ ያስፈልግ ነበር። ሆኖም ግን በሃገር ፍቅር ስሜት የተነሱት ዘጠኙ ወጣቶች ማለትም አየለ አትናሽ፣ ጆርጅ ዱካስ፣ ዮሐንስ ጥላሁን፣ ገብረመድህን ተፈሪ፣ ተፈራ ገብረእግዚአብሔር፣ ዓለማየሁ እጅጉ፣ መኮንን ደምሴ፣ አስፋው ያዕቆብ እና ክልቱ አያኖ ክለቡን በሚመሰርቱበት ወቅት ቤሳ ቤስቲን እንኳ ኪሳቸው ውስጥ ስላልነበራቸው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ተሰብስበው በሰፊው ተወያዩ። በዚህ የውይይት ወቅት ነው ገንዘብ ለማግኘትና የክለቡን መመስረት እውን ለማድረግ የቡሄ ቀን እጅግ መልካምና ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን የተረዱት። ዘጠኙ ወጣቶች በአንድ ድምፅ ተስማምተው በታሪካዊው የቡሄ ዕለት ማለትም ነሐሴ 13 ቀን 1927 ዓ.ም. በጋራ በመሆን ቡሄ ጨፍረው (ሆያ ሆዬ ብለው) በሚያገኙት ማናቸውም ነገር የክለቡን የመጀመሪያ ማሊያ ለመግዛት ቁርጥ የሆነ ውሳኔ ላይ ደረሱ። በዚያን ጊዜ የነበረው የባህል ልማድ አሁን ካለው የተለየ በመሆኑ፣ ቡሄ ሲጨፈር የሚሰጠው ጥሬ ገንዘብ ሳይሆን ሙልሙል ዳቦ ነበር። በመሆኑም ዘጠኙ ተጫዋቾችና መስራቾች ቀደም ሲል ከሚጨፍሩበትና ለምደውት ከነበረው አካባቢ ራቅ ብለው በመንቀሳቀስ በየቤቱ በር እያንኳኩ በደመቀ ሁኔታ ጨፈሩ፤ በዚህም ጥረታቸው በርካታ ቁጥር ያለው የሙልሙል ዳቦ በአንድነት ማሰባሰብ ቻሉ ታሪካዊውን ስራ ሰሩ። ይሁን እንጂ የተሰበሰበውን ይህንን በርካታ ዳቦ ወደ ጥሬ ገንዘብ ለመቀየር አዲስ አበባ ውስጥ ወደሚገኘው ሰራተኛ ሰፈር ለሚገኙ ወዛደሮች ለመሸጥ ዳቦውን በከረጢት ይዘው ጉዟቸውን ጀመሩ። በዚህ የጉዞ መስመር ላይ ሳሉ ግን ያልተጠበቀ ፈተና ገጠማቸው፤ በመንገድ ላይ ያገኟቸው “ዱርዬዎች” ከተሰበሰበው ዳቦ ላይ የተወሰነውን ነጠቋቸው። ወጣቶቹ ተስፋ ሳይቆርጡ ጉዟቸውን በመቀጠል የተረፈውን ዳቦ ለሰራተኛ ሰፈሩ ወዛደሮች በመሸጥ ማሊያ መግዣ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ በእጃቸው አስገቡ። ከዳቦው ሽያጭ የተገኘችው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን በወቅቱ መገበያያ በትክክል ሁለት ጠገራ ብር ነበረች። የክለባችው የመጀመሪያ መለያ ቡናና ነጭ ነበር። ቡናና ነጭ መሊያን የገዙት ግን ፈልገው አልነበረም በቂ ገንዘብ ስላልነበራቸው በሁለት ጠገራ ብር ከፒያሳ «ግሪካዊ አውግስታስ ዱስ» ከተባለ ሱቅ በርካሽ ስላገኙት ነበር። ይህ በቡሄ ዕለት የተጀመረው ታሪካዊ የማሊያ ግዢ በኋላ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በታህሣሥ ወር 1928 ዓ.ም. በይፋ ተመሠረተ። ክለቡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለብ በመሆን ታሪካዊ ማዕረግንና ቀዳሚነትን ተቀዳጀ። በ1928 ዓ.ም. በይፋ የተመሰረተው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በታሪኩ የመጀመሪያውን የሜዳ ጨዋታ ያደረገው ከ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ነበር። በዚሁ ታሪካዊ የመጀመሪያ ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። በዕለቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠንካራ ተፎካካሪ ከነበረው የ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ለመጫወት ወደ ሜዳ ሲያመራ፣ አስቀድመው ከተመረጡትና ቡድኑን ካደራጁት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ባልታወቀ ምክንያት ሳይመጣ ቀረ። በዚህ ድንገተኛ መቅረት ምክንያት ቡድኑ በሰው ጎደሎ ለመጫወት በተገደደበት ወሳኝ ሰዓት፣ መስራቾቹ በሜዳው አቅራቢያ መንገድ ላይ ሲጫወት ያገኙትን አንድ ታዳጊ ወጣት ተመለከቱ። ይህ ታዳጊ በወቅቱ ገና የ14 ዓመት ዕድሜ የነበረውና በኋላ ላይ የኢትዮጵያ ስፖርት ባልደረባ የሆነው ይድነቃቸው ተሰማ ነበር። ወጣቶቹም ያለ ምንም ቅድመ ዝግጅት ቡድኑን እንዲሞላ ድንገት ጋበዙት፤ እርሱም የቀረበለትን ጥሪ በደስታ ተቀብሎ በአጋጣሚ ወደ ሜዳ ገባ። ያለ ምንም ልምምድና ዝግጅት በድንገት የተሰለፈው ይድነቃቸው ተሰማ፣ በሜዳ ላይ ያሳየው አስደናቂ ችሎታና ቅልጥፍና ሁሉንም ያስገረመ ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ታሪካዊ ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ፣ ለክለቡ የመጀመሪያውን ድል ያስገኙትን ሁለቱንም ታሪካዊ የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ይኸው መንገድ ላይ ተገኝቶ በድንገት የተሰለፈው ታዳጊ ይድነቃቸው ነበር። ይህ ብቃት ገና በታዳጊነቱ በክለቡ ውስጥ ያለውን የማይተካ ቦታ ከማረጋገጡም በላይ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን የድል ጉዞ በደመቀ ሁኔታ እንዲጀመር አድርጓል። ቡሄ በዓል እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ያላቸው ታሪካዊ ቁርኝት የክለቡን ጥልቅ ህዝባዊና ባህላዊ መሰረት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቀዳሚ ፋና ወጊ የሆነው ይህ ታላቅ ክለብ፣ በታሪካዊቷ የነሐሴ 13 ቀን የቡሄ ዕለት የመስራቾቹ የ"ሆያ ሆዬ" ጨዋታና ከተሰበሰበው ሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ባገኟት ሁለት ጠገራ ብር የመጀመሪያውን ቡኒና ነጭ ማሊያ መግዛቱ፣ ክለቡ ከህዝብ ማህፀን የወጣ የህዝብ ሀብት መሆኑን ያረጋግጣል። ይህ ከባህልና ከትውፊት ጋር የተቆራኘ አስደናቂ አጀማመር፣ ከጊዜ በኋላ በ1928 ዓ.ም. ለይፋዊ ምስረታው በር ከፋች ከመሆኑም በላይ፣ በታሪካዊው የመጀመሪያ ጨዋታ ላይ እንደ ይድነቃቸው ተሰማ ያሉ የአፍሪካ እግር ኳስ ታላላቅ መሪዎችና ድንቅ ተሰጥኦዎች እንዲፈጠሩ መሰረት የጣለ የኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ነው።
ቡሄ የትውልድ ወጋገን፤ የማኅበራዊ ትስስር አምድ
Aug 19, 2026 258
ቡሄ በወርሃ ነሐሴ በ13ኛው ቀን ህፃናት ሆያ…. ሆዬ….! ሆ…. በሚል ዜማና ጅራፍ እያጮሁ የሚያከብሩት፤ እናቶች ለህፃናቱ ሙል ሙል ዳቦ በመስጠት እንኳን አደረሳችሁ እያሉ በድምቀት የሚያከብሩት በዓል ነው። ቡሄ ትርጓሜውም ብርሃን፣ብራ፣ ወጋግን ማለት ሲሆን ከጨለማ ወደ ብርሃን የመሸጋገሪያ የተስፋ ምልክት ነው። በሀይማኖታዊ አንድምታው በዓሉ የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ ብርሃን በደብረ ታቦር ተራራ ላይ መገለጡ የሚታሰብበት ነው፤ በዚህም ደብረ ታቦር ይባላል፡፡ የክረምቱ ጭጋግ ተገፎ የብርሃን ወጋገን የሚታይበት ሕፃናትና ወጣቶች በየቤቱ እየዞሩ «ሆያ ሆዬ» በማለት በረከትና ምርቃት የሚያፍሱበት የደስታና የፍቅር መግለጫ ነው። ህፃናትና ወጣቶች በየዕድሜያቸው ጅራፍ እያጮሁ በሕብረ ዝማሬዎች እየደመቁ በአብሮነት እና በደስታ የሚያከብሩት ትውፊታዊ በዓል ነው ቡሄ። የወጣቶችን ጉርብትና እና ማኅበራዊ ትስስር የሚያጎለብት እሴት ነው፤ በአከባበሩ ወቅት የሚንጸባረቀው የመረዳዳትና ያለውን የመካፈል ባህል ፋይዳውን ከትውልድ ወደ ትውልድ ማሸጋገር ያስችላል። የቡሄ በዓል ባህላዊ እሴቶችን በመጠበቅ፣ ትውልድን በማቀራረብ እና ማኅበራዊ ትስስርን ይበልጥ በሚያጠናክር ተምሳሌትነቱ እልፍ ነው። በአዲስ አበባ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከፍተኛ የቅርስ ጥናት ተመራማሪ መምህር መክብብ ገብረማሪያም ለኢዜአ እንዳሉት፤ የቡሄ በዓል የብርሃን ዘመን መምጣቱን የተስፋ ጎህ መቅደዱን ማብሰሪያ ነው፡፡ ቡሄ ከጨለማ ወደ ብርሃን ሽግግር መምጣቱን የሚያበስር በታዳጊዎች የሚዘከር የፍቅር፣ የአንድነትና የበረከት መገለጫና ተስፋ መሆኑን ያነሳሉ፡፡ ታዳጊዎችና ወጣቶች በበዓሉ ወቅት የሚያዜሙት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሸጋገር የመጣው የ«ሆያ ሆዬ» ሕብረ ዜማ ለጋራ ትርክት ግንባታ ገንቢ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል። ቡሄ የትውልድ ወጋገን፤ የማኅበራዊ ትስስር አምድ በመሆኑ ማኅበራዊ ትስስርና የጋራ ዕሴቶችን ማጠናከር ያስችላል ብለዋል።   ታዳጊው በሱፈቃድ አስሜ ቡሄ ከጓደኞቹ እና ከወዳጅ ዘመዶቹ ጋር ፍቅርንና አብሮነትን ይበልጥ የሚያጠናክርበት የደስታና የተስፋ በዓል መሆኑን ይናገራል፡፡ ቡሄ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠብቀውና ቀጣይ ሕይወቱን በአዲስ መንፈስ ለመምራት አቅም የሚፈጥርለት የብሩህ ዘመናትን ማለሚያ መሆኑን ይገልፃል። ቡሄ ከታላላቆቹ የወረሰው ከእኩዮቹ ጋር በፍቅርና በደስታ የሚያከብረው ነገን በተስፋ የሚያይበት ውብ በዓል እንደሆነ የሚናገረው ደግሞ ታዳጊው በረከት ምናለ ነው፡፡   የተጣሉ ጓደኛሞች እርቅ የሚያወርዱበት በዓል በመሆኑ ለትውልድ አንድነት እና አብሮነትን በማስተማር ረገድ ትልቅ ድርሻ አለውም ብሏል። ወጣት ያብስራ ጸጋዬ በበኩሉ ቡሄ በዓመት አንድ ጊዜ የሚመጣ፤ ተራርቀው ከሚኖሩ የተለያዩ አካባቢ እኩዮቹ ጋር በአንድነት የሚያከብሩት በዓል መሆኑን ይናገራል፡፡   ከሁሉም ዓይነት ሕብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ታዳጊዎች የሚሰባሰቡበት፤ ሕብረ ብሔራዊነትን የሚያጠናክር የጋራ በዓል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ በኃይሉ ሞገስ ናቸው።      
ሳምንቱን በወፍ በረር!!
Aug 16, 2026 233
ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ሳምንቱን በወፍ በረር!! በዚህ ዝግጅታችን በክልሎች የተከናወኑ ዓበይት ጉዳዮችን በወፍ በረር ቃኝተን እናስታውሳለን። በመሆኑም በሳምንቱ በተለያዩ የሀገራችን ክልሎች ከተከናወኑ ዓበይት ኩነቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ ምን ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 1. የሰሊጥ ልማት በጋምቤላ ከሳምንቱ ዓበይት ጉዳዮች መካከል በጋምቤላ ክልል በተያዘው የመኸር ወቅት ከ86 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥ ሰብል የመልማቱ ዜና አንዱ ነው። በክልሉ የቅባት እህሎች ልማት በዋናነት በባህላዊ አርሶ አደሮችና በጥቂት ባለሀብቶች ተወስኖ ሲከናወን የነበረ ቢሆንም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመናዊ የግብርና ግብዓቶች እና በሜካናይዜሽን እርሻ ታግዞ እየተካሄደ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታውቋል።   እንደ ቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ኡጀሉ ኡሞድ ገለጻ፤ ክልሉ የቅባት ሰብሎችን ጨምሮ ለሁሉም የግብርና ልማት ሥራዎች ምቹ ስነ-ምህዳር ያለው ነው። በክልሉ በዘንድሮው የመኸር ወቅት በባለሀብቶችና በአርሶ አደሮች ከ86 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥ ሰብል ለምቷል። ከዚህም ከ516 ሺህ ኩንታል በላይ የሰሊጥ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቁመው፣ በአሁኑ ወቅት የሰብሉ ቁመና በተሻለ ሁኔታ ላይ ስላለ ከተጠበቀው በላይ ምርት ሊገኝ እንደሚችልም ተንብየዋል። 2. የገቢ አሰባሰብን በማጠናከር ልማትን ማፋጠን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝብን የልማት ጥያቄ የመመለስ ተግባራት እንደሚጠናከሩ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የተገለጸውም በዚህ ሳምንት ነበር።   ርዕሰ መስተዳድሩ ይህን የተናገሩት የክልሉ ገቢዎች እና ንግድና ገበያ ልማት ቢሮዎች በሕገ-ወጥ የንግድ ቁጥጥር፣ ኑሮን ማረጋጋትና የታክስ ሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ በሆሳዕና ከተማ ባዘጋጁት የንቅናቄ መድረክ ላይ ነው። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች የመመለስ ተግባር እንደሚጠናከር ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ገቢን በማሳደግ የከተሞችን ገጽታ የመቀየር፣ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን የማስፋትና የማህበረሰቡን ሕይወት ለማሻሻል በተከናወኑ ተግባራት ስኬቶች እንደተመዘገቡና በቀጣይም ይህን ለማጠናከር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል በክልሉ የንግድ ሥርዓቱን በማዘመን የተሳለጠ አሠራር መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን የጠቆሙት እንዳሻው (ዶ/ር)፤ ለዚህም ሕገ-ወጥነትን የመከላከል፣ የግብይት ማዕከላትን የማስፋፋት፣ ምርትን በበቂ ሁኔታ የማቅረብ፣ የዋጋ ንረትን የመቆጣጠርና የሸማች ማኅበራትን የማጠናከር ሥራዎች እንደሚከወኑም አክለዋል። 3. የአፋር ክልል በጀት የክልሉ ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ33 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ያጸደቀውም በዚሁ ሳምንት ነበር። በሰመራ ከተማ ለሦስት ቀናት የተካሄደው የምክር ቤቱ 6ኛ የምርጫ ዘመን፣ 5ኛ የሥራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባዔ የዳኞችንም ሹመት አጽድቋል።   የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደረሳ መሐመድ በጉባዔው ተገኝተው የክልሉን የ2019 ረቂቅ በጀት ያቀረቡ ሲሆን፣ በጀቱ ከመንግሥት ድጎማ፣ ከክልሉ የውስጥ ገቢ፣ ከፌዴራል መንግሥት እና ከተለያዩ የገቢ አማራጮች የሚሸፈን መሆኑን አንስተዋል። ለበጀት ዓመቱ የተመደበው ገንዘብ የክልሉን ልማት ለማቀላጠፍና የሕዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል ከመሆኑም በላይ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ይረዳል ብለዋል። 4. የኢንቨስትመንት መድረክ ሌላው የሳምንቱ ዓበይት ጉዳይ የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈጻሚ አካላት በጋምቤላ ከተማ ያካሄዱት የጋራ የምክክር መድረክ ነበር። በመድረኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የኢንቨስትመንት እድሎችን በማስተዋወቅና ቀልጣፋ የአሰራር ስርዓቶችን በመተግበር በርካታ ባለሀብቶችን ወደ ሀገር ውስጥ ለመሳብ መቻሉም ተገልጿል።   በመድረኩም ሀገሪቱ ያሏትን የኢንቨስትመንት እድሎች ለባለሀብቶች የማስተዋወቅ እና አገልግሎቶችን ቀልጣፋ ለማድረግ የተሰሩ ሥራዎች ውጤት ማምጣታቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል። የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዳጋቶ ኩምቤ በመድረኩ እንደገለጹት የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ አልሚዎችን ለመሳብ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ ነው። በዚህም በበጀት ዓመቱ ብቻ 528 የውጭ ሀገር ባለሀብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን በማሳያነት አንስተዋል። 5. የወጣቶች ተሳትፎ የላቀበት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በየአካባቢው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው የተገለጸው በዚሁ ሳምንት ነበር። በጅማ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካሞች ቤት ዕድሳት እና ሌሎች የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎችን ለማከናወን በተዘጋጀ መርሃ ግብር ላይ የአቅመ ደካማ ወገኖችን ሕይወት በዘላቂነት ለመቀየር ያለመ ድጋፍ ተደርጓል። ከድጋፎቹ መካከል የትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ፣ የምግብ ግብዓት፣ የንብ ቀፎዎች እና ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ምጣድ ይገኙበታል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ረሂማ ዩሱፍ፣ በክልሉ በርካቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውንና በአገልግሎቱም የወጣቶች ተሳትፎ የላቀ መሆኑን ተናግረዋል። የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ በተያዘው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በዞኑ ከ5 ሺህ 500 በላይ አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤትን ለማደስ መታቀዱንና እስካሁንም ከግማሽ በላይ የሚሆኑት መታደሳቸውን አንስተዋል። 6. ሚኒስቴር ተቋማቱ በበጎ ፈቃድ ተግባር ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አቅመ ደካማ ለሆኑ ወገኖች ልጆች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ያደረገውም በዚህ ሳምንት ነበር። ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን እንደገለጹት፤ ድጋፉ የተደረገው በሐረር ወላጆቻቸው አቅም ለሌላቸው 600 ተማሪዎች ነው። ሚኒስትር ዴኤታው ከሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ዑመር ጋር በመሆን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ያከናወኑ ሲሆን፣ በክልሉ የአቅመ ደካማ ዜጎች መኖሪያ ቤት ግንባታንም አስጀምረዋል። ሚኒስቴሩም ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ክልሎች መሰል የልማት ሥራዎችን በማከናወን ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን አስታውሰዋል።   በተመሳሳይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ በተያዘው ሳምንት ነበር በዱብቲ ወረዳ አሮላፍና ገበላይቱ ቀበሌ የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤቶች ግንባታና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ያከናወኑት። በዚህ ወቅትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታው አምባሳደር ብርሐኑ ጸጋዬ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በተቀናጀ መልኩ ማከናወኑ ማህበራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስቴሩም በዘንድሮው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በአፋር ክልል 10 የአቅመ ደካማ ወገኖች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እያከናወነ መሆኑን አንስተው፣ በተጨማሪም አንድ የቅድመ መደበኛ መዋዕለ ሕፃናት ትምህርት ቤት እንደሚገነባም ነው የገለጹት። 7. የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ውጤታማነት ሳምንቱ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማነት ማሳደጉ የተገለጸበትም ነበር። የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ መንግሥት በተለይ የመሬት፣ የኤሌክትሪክ፣ የፋይናንስ፣ የመሠረተ ልማት እና ሌሎች ጥያቄዎች በአፋጣኝ እንዲመለሱ መደረጉ ኢንዱስትሪዎቹ ውጤታማ እንዲሆኑ አስችሏል ብለዋል።   በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ 11 ከፍተኛ እና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ በመግባት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል። ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ የወጪ ምርቶችን አምርተው በመላክ ለሀገር የውጭ ምንዛሬ እያስገኙ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ጉብኝት ከተደረገባቸው አምራች ኢንዱስትሪዎች መካከል የፈሳሽና ጠጣር ሳሙና፣ የጭማቂ፣ የውሃ፣ የሮቶ፣ የካርቶንና የእርሻ መሳሪያ ማምረቻዎች እንዲሁም የቡና ማቀነባበሪያዎች ይገኙበታል። 8. ሠራዊቱ ከወገን አለኝታነቱ ባሻገር የልማት አጋርነቱን አጠናክሯል ከሳምንቱ ዓበይት ጉዳዮች መካከል የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ዳር ድንበር የማስከበር ግዳጁን ከመወጣት ጎን ለጎን የወገን አለኝታነቱንና የልማት አጋርነቱን የሚያጠናክሩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑም በዋነኝነት የተገለጸበት ነው። በሀገር መከላከያ ሠራዊት የ11ኛ ዕዝ አመራሮችና የሰሜን ወሎ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በቆቦ ከተማ እየተካሄደ ያለውን የኮሪደር ልማት ጎብኝተዋል። የ11ኛ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አድማሱ ዓለሙ በወቅቱ እንዳሉት፤ የቆቦ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቅ ዕዙ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል። በዚህም የዕዙ አመራሮችና አባላት የኮሪደር ልማቱን ለማፋጠን የወር ደመወዛቸውን 40 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።   ድጋፉም ሠራዊቱ የአካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ለልማት ሥራው ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር ባሻገር የወገን አለኝታነቱን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። የዕዙ አመራሮችና አባላት ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡት የቆቦ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኃይለዓብ ወንድሙ፣ ድጋፉ አሁን ላይ 43 በመቶ የደረሰውን የኮሪደር ልማት ፈጥኖ በማጠናቀቅ ለህዝብ አገልግሎት ለማብቃት ያስችላል ብለዋል። 9. ኢትዮጵያን በመገንባት ረገድ የወጣቱ ሚና ወጣቱ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ሁለንተናዊ ተሳትፎውን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ያሳሰቡትም በዚሁ ሳምንት ነበር።   ከንቲባው ይህን ያሳሰቡት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ27ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ23ኛ ጊዜ በድሬዳዋ በተከበረው ዓለም አቀፉ የወጣቶች ቀን ላይ ተገኝተው ነው። በመልእክታቸውም ወጣቶች የተሻለች ሀገርን ለመገንባትና ለመረከብ እያደረጉት ያለው ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት አበረታች ውጤት እየተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። ወጣቶች በተለይም የውሳኔ ሰጪነት ሚናቸውን ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ሀገር ተረካቢ የሆነውን ትውልድ ወደ ላቀ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እንደሚያሸጋግርም በመድረኩ ተገልጿል። 10. ዲጂታላይዜሽንን ለሙስና መከላከል የመደመር መንግሥት የፈጠራቸውን መልካም እድሎች በመጠቀም ለሀገር ልማት በጋራ መትጋትና ልሹ አሰራሮችን መዋጋት እንደሚገባ የተገለጸው በተያዘው ሳምንት ነው። የፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓል ማጠቃለያ መድረክ "የፀረ-ሙስና ትግል ትናንት፣ ዛሬ እና ነገ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዳማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቴ አለነ፤ በሙስና ትግል የመጀመሪያ ምዕራፍ መከላከልን፣ ምርመራንና ክስን በአንድ ተቋም በማድረግ ይሰራ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም እንቅስቃሴው ህዝብን የትግሉ ባለቤት ያላደረገ፣ የሙስና መከላከል ስራን የረሳ እና ለትውልድ የስነ-ምግባር ግንባታ ቦታ የማይሰጥ ነበር ብለዋል።   በሁለተኛው ምዕራፍ፣ ከሚሊኒየም መባቻ ጀምሮ ለውጡ እስከመጣበት ጊዜ ድረስ የነበረው ወቅት በልማታዊ መንግሥት ስም ከፍተኛ ጣልቃገብነት የተካሄደበት እንዲሁም ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ የተስፋፋበት እንደነበር አንስተዋል። በዚህም ምክንያት የህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ ሜጋ የመንግሥት ፕሮጀክቶች በሙስና እና በሌብነት ምክንያት ለከፍተኛ ችግር ተዳርገው እንደነበር አስታውሰዋል። በሦስተኛው ምዕራፍ፣ ከሀገራዊ ለውጡ መባቻ ጀምሮ እስካሁን ባለው ጊዜ ከሙስና ትግል አኳያ መሰረታዊ ለውጥ ተደርጓል ብለዋል። በኮሚሽኑ ላይ ከተደረጉት ማሻሻያዎች መካከል ዋነኛው የሕግ ሪፎርም መሆኑን አንስተው፤ ሙስናን በአንድ ተቋም ብቻ መታገል ስለማይቻል ሁሉም የመንግሥት ተቋማት የትግሉ ባለቤት እንዲሆኑ መደረጉን አስታውቀዋል። በተለይም የዲጂታላይዜሽንን መልካም እድሎች በመጠቀም አገልግሎቶችን ከሰው ንክኪ ነፃ እና አካታች በሆነ መንገድ ማቅረብ መቻሉና መሰረታዊ የእሳቤ ለውጥ ማምጣቱ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ጠንካራ መሰረት እየጣለ መሆኑን አክለው ገልጸዋል። 11. ኢዜአ በበጎ ፈቃድ ተግባር ላይ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ባደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደሰታቸውን በባህር ዳር ከተማ ድጋፍ የተደረገላቸው ተማሪዎችና ወላጆች መግለጻቸው የተዘገበውም በሳምንቱ ነበር።   በወቅቱም የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተፈራ በቀለ፤ ኢዜአ ከመረጃ ተደራሽነት ባሻገር በማህበራዊ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ አገልግሎት በስፋት እየተሳተፈ መሆኑን ገልጸዋል። ኢዜአ የትምህርት ቤቶች ድጋፍ ላለፉት ስድስት እና ሰባት ዓመታት በተከታታይ ሲያከናውን መቆየቱን አንስተው፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ በትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍና በመሰል በጎ ተግባራት ተሳትፎውን አጠናክሮ መቀጠሉንም አክለዋል። በበባሕር ዳር ከተማ የአረንጓዴ አሻራን ከማኖር ባለፈ ኢዜአ ለ357 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉንም ገልጸዋል። የባሕር ዳር ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አስራቴ ሙጨ በበኩላቸው፤ የኢዜአ አርዓያነት ያለው ተግባር በሌሎችም ዘንድ መቀጠል ያለበት መሆኑን ገልጸው፤ ለተደረገው መልካም ተግባር ሁሉ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ስም ምስጋና አቅርበዋል። ድጋፍ የተደረገላቸው ተማሪዎችና ወላጆች ኢዜአ ባደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸው ለተደረገውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ ከትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በተጨማሪ በባህርዳር የመዋዕለ ሕፃናት ትምህርት ቤት የሕንፃ ግንባታን አስጀምሯል። የሚገነባው የመማሪያ ክፍል ለታዳጊ ተማሪዎች ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል ሲሉ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ የገለጹትም በዚህ ወቅት ነው።   የኢዜአ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ምንይችል ዓለማየሁ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ በገጽታ ግንባታ ሥራዎች እንዲሁም የጋራና አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሀገራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።ተቋሙ ከሀገራዊ ተልዕኮው ባሻገር በማኅበራዊ ተሳትፎና የበጎ ፈቃድ ተግባራት ላይም ሰፊ ተሳትፎ በማድረግ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። ኢዜአ በባሕር ዳር ከተማ ምስራቀ ፀሐይ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቅድመ መደበኛ ትምህርት አስተባባሪ መምህርት አያል እምቢያለ፤ በአሁኑ ወቅት በአንድ ክፍል ውስጥ እስከ 150 ተማሪዎች እንደሚማሩ አስታውሰዋል። አዲሱ የመማሪያ ሕንፃ ግንባታ ይህንን የተማሪዎች የክፍል ጥምርታ በማስተካከል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል። ከዚሁ መርሃ ግብር በተጓዳኝም የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀንን ምክንያት በማድረግም ከወጣቶች ጋር የፓናል ውይይት ተካሂዷል።              
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር!
Aug 9, 2026 881
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር! በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን ) የገጠሩ ማህበረሰብ የጨለማ ኑሮ የተፈረደበት ይመስል ኑሮውን ማሻሻል ሳይችል እልፍ ዓመታት ተቆጥረዋል፤ ለዘመናት መብራትና ውኃ ለማግኘትና ከቴክኖሎጂ ጋር ተቀራርቦ ለመኖር ወደ ከተማ መሰደድ ብቸኛው አማራጭም ነበር። የከተሜው ዋልታ የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት የሚወሰንበት የአራሹ ገበሬ የኑሮ ደረጃ ባህላዊውን የአኗኗር ዘዬ ባለመልቀቁ ደስተኛ ጊዜ የሚያሳልፍበት ሂደት አድካሚ እንደሚሆን ግልጽ ነው። የገጠሬው የተበታተነ የአኗኗር ሥርዓትም ለገጠሬው አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፤ የእዚህን የህብረተሰብ ክፍል ምርቱን እንጂ ኑሮውን የጠየቀ አልነበረም ቢባል ግነት አይሆንም።   ቀደም ሲል በነበሩ መንግስታት ከተማን እንጂ ገጠርን ማዘመን የሚያስብ ስለመኖሩ ያጠራጥራል፤ ይህም በሀገሪቱ ለኢፍትሐዊ ዕድገት የራሱን ተጽዕኖ ሲያሳደር ቆይቷል። የመደመር መንግሥት ግን ይህን ቀይሮታል። ሀገር የመምራት ኃላፊነት ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ በከተማና በገጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ በዜጎች የኑሮ ሥርዓት ላይ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርጎ እየሰራ ነው ከተሜነት ብቻውን አድጎ የገጠሩ ማኅበረሰብ በቀድሞ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሆነ የተሟላ ዕድገት ማምጣት አይቻልም የሚል ጽኑ እምነት አለው። በእዚህም ከተማና ገጠርን ለማቀራረብ በገጠር ትራንስፎርሜሽንን የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ቀርጾ መተግበር ከጀመረ ከራርሟል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን አንዱ አካል የሆነው የገጠር ሞዴል መንደር በአርሶ አደሮች ዘንድ የሚጨበጥ ተስፋን ይዘው ከመጡ ኢኒሼቲቮች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። ከተስፋ ተሻግረው በዚህ ሞዴል መንደር የነዋሪነት ዕድልን ያገኙት ደግሞ ብርሃን አይተዋል፤ የትናት አኗኗራቸውን የቀየረ አዲስ ዛሬን በእጃቸው አድርገዋል፤ ነገን አልቀው መመልከት የግብርና ተግባራቸው አንዱ አካል ሆኗል። በአዲሱ መንደራቸው ዛሬ የሚያፈስ ቤት የለም፣ የእንስሳት ቆሻሻ ሽታ በአፍንጫቸው አይገባም፣ በሚቆረቁር እንጨት ወይም መደብ ላይ አይቀመጡም፤ የከተሜው መዘነጫ ሶፋ በሳሎናቸው ተከስቷል። ጓሮዎቻቸው ሁሉ ሙሉ እንደሆኑ አፍ አውጥተው የሚያወሩ ናቸው። በዚህ ቆስጣ፤ በዛ በኩል ጎመንና ቀይስር፤ ዘውር ሲሉ ደግሞ ከአስር የሚልቁ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፤ በአንድ ክፍል ደግሞ እናት ላም ከጥጃዋ ጋራ፣ የእንቁላል ዶሮ ከሥጋ ዶሮ ጋር ሁሉንም በአንድ ጊቢ ውስጥ ያገኛሉ። ምን ይሄ ብቻ አቮካዶ እና ፓፓያ፣ ሙዝና እንሰት፣ በርበሬና ሽንኩርት ሳይቀር ለተትረፈረፈ የአርሶ አደር ማዕድና ገበያ ራሳቸውን አዘጋጅተዋል።   አርሶ አደር ኃይሉ ሞትንሞስ በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ ናቸው። እርሳቸው "መንግስት ጨለማችንን ገፎ ብርሃን አሳየን" ሲሉ በጠንካራ ቃላት የገጠር ሞዴል መንደር ፕሮጀክት ያመጣላቸውን በጎ ነገር ይገልጻሉ። እውነት ነው ያላዩትን ብዙ ነገር አሳይቷቸዋል። ያም ብርሃን ቤት ውስጥ የሚበራ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው፣ በነገ ተስፋቸውና በኢኮኖሚያቸው ላይ የፈነጠቀ ብርሃን ነው። ዛሬ ያሉበትን ህይወትም "ለእኔ አዲስ ነገር ነው። አይቼው አላውቅም፤ መቼም በራሴ ሀሳብ አላደርገውም ነበር።" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግስት አበራልኝ ያልኩት በእጄ ያለኝን ያላየሁትን ዕድል ስላሳየኝ ነው በማለትም ሀሳባቸውን ይቀጥላሉ። እኛ ሀብት አለን፤ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም። ይልቁንም የምናባክነው ይበዛል በማለትም የቀደመ ሕይወታቸውን እያሰቡ ይቆጫሉ። አሁን ግን ብዙ ተገነዘብኩ የሚያስብል የመደመር መንግስት በመኖሩ አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። እርግጥ ነው የገጠር ሞዴል መንደር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ነው። ለአብነትም የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ማንሳት ይቻላል። የተሠሩ ሞዴል መንደሮች በመጀመሪያ የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ የመሆን ዕድል ገጥሟቸዋል። በመቀጠል ንጽሕናው ያልተረጋገጠ የመጠጥ ውኃ ወንዝ ወርዶ ከመቅዳት ተቆጥበው በመንደራቸው የተገነባውን የከረሰ ምንድር ውሃ ከቧንቧ ቀድተው መጠጣት አስችሏቸዋል። በእሳት እና ኩራዝ ጭስ ሲሰቃዩ የነበሩ ዓይኖቻቸው ዛሬ ከሶላር ቴክኖሎጂ የመነጨ ብርሃን ማየት ጀምረዋል። ብርሃን ብቻ አይደለም ለወትሮ ለገበያ ወደ ከተማ ብቻ ሲወጡ ይመለከቱ የነበረውን ቴሌቪዥን ዛሬ በቤታቸው አስገብተው የመረጃና የመዝናኛ ዓለምን ተቀላቅለዋል። አርሶ አደሮቹ ቴሌቭዥንን ከመዝናኛነት ይበልጥ ለመረጃ እንደሚጠቀሙት ያነሳሉ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በዜና ተከታትሎ መረዳት፣ የገበያ ሁኔታን ማወቅ፣ የግብርና ሥራ ተሞክሮን መቅሰምና የአየር ንብረት ሁኔታን ጨምሮ ለሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙት ከቴሎቪዥን መስኮት እንደሆነ ይናገራሉ።   በጓሯቸው የተትረፈረፈ የሌማት ትሩፋት ምርት መሰብሰብ የሚያስችላቸው ምቹ ሁኔታ ደግሞ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው። በተለይ መንግስት በጓሯቸው ጥምር እርሻ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የነገ ኢኮኖሚያቸውን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ ነው። ከተማን መናፈቅን ያስቀረው የገጠር ሞዴል መንደር ያኔ ከጅምሩ አመኔታን አላገኘም። የቦታና የአካባቢ ቁሳቁስ ለማቅረብ ዝግጁ እስካለመሆን የደረሱ አርሶ አደሮችም ነበሩ። በወቅቱ ጉዳዩን እንደፌዝ አዩት። ዛሬ ግን ውጤቱን በአግራሞት በዐይናቸው ተመለከቱ። የተናገረውን የሚከውን፤ የጀመረውን የሚጨርስ የመደመር መንግሥትን ተጨባጭ ስራዎች በማረጋገጥ እንደ ትንግርት ቆጠሩ። ዛሬ በየአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በቁጭት ተሞልተው መንደራቸውን ወደዚህ የሞዴል መንደር እሳቤ ለመቀየር ተነሳስተዋል። የጌሊት ቀበሌ አርሶ አደሮቹ መኮንን አርዶ እና ነጻነት ተስፋሁን ለዚህ ተጠቃሾች ናቸው። ያዩትን ተሞክሮ በራስ አቅም በመንደራቸው ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ከተማ ሄደን የምናወጣውን ወጪና የምናባክነውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት እዚሁ መዝናናት የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል።   "ይህ ዕድል ለእኛ ለአርሶ አደሮች በታሪክ የሚነገር ትልቅ አጋጣሚ ነውም" ይላሉ። በጤዛ እየራስን እንጓዝበት የነበረው መንገዳችን ዛሬ ሰፍቷል። ተሽከርካሪ በደጃችን ስለሚያልፍም ምቹ ዕድልን ይዞልን መጥቷል። ይህን ጅምር ተግባር ወደ ላቀ ውጤት ማሸጋገር የእኛ ድርሻ ነውና ጠንክረን እንሠራለንም ብለዋል።   ይህን ዕድል ወደ ትልቅ አቅም ለመቀየር መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ የሸሸቃ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር አልዓዛር ዘርክናንስ ናቸው። የዶሮና የከበት እርባታን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ ሥራን ከመደበኛው የእርሻ ሥራ ጋር አስተሳስረው በመሥራት ከቤተሰብ ፍጆታ ተርፎ ለገበያ የሚበቃ ምርት ለማምረት እየተዘጋጁ ነው።   ይህም የገቢ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ልጆቻቸው ወተትና የወተት ተዋጽኦ በቤታቸው እንዲያገኙ ያደርጋል። ማር፣ እንቁላል እና ሥጋ እንዳያምራቸው የሚያደርግ ትልቅ ኢኒሼቲቭም ነው። አንዱ ቢጎድል በሌላው እየሞሉ የሚኖሩበትን የሥራ መስክ አጠናክረው ለውጤት አብቅተው ለተሻለ ለውጥ እንደሚሠሩ አክለዋል። የአርሶ አደር እናቶች ዘምቢል ይዘው አትክልትና ፍራፍሬ ሸመታ ወደ ገበያ ማቅናት የለባቸውም። ይልቁንም ከጎሮቸው ወደ ገበያ ይዞ መውጣት የኑሮ ዘዬያቸው ወግ ነው። ወይዘሮ መሠረት ማሞ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ያልለመዱትን አዲስ ሕይወት ከአዲስ ተስፋ ጋር መጀመራቸውን ከሚናገሩት መካከል ናቸው።   ትናንት ኩሽናቸው፣ መኝታቸው እንዲሁም የከብትና የዶሮ ማደሪያ በአንድ ቤት ወስጥ የተወሰነ እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን ሽንት ቤትና መታጠቢያ ቤት ሳይቀር ለየብቻ የራሱ የሆነ ቤት ተገንብቶ ጽዳቱ የተጠበቀ ኑሮ መኖር ጀምረዋል። ቤታቸው ሲገቡና ሲወጡ ለዓይን ማራኪ፤ ለመቀመጥ ምቹ፤ ለመተኛትም ንጹህና ወገብ የሚያሳርፍ ሆኖ አግኝተዋል። እናም በዚህ እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። "መንግስት እንደ አባት ጎዶሏችንን ሞልቷል" ሲሉም ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ የአርሶ አደሮችን ሕይወት ብሩህ ያደረገው የገጠር ሞዴል መንደር ኢኒሼቲቭ በመላው ሀገሪቱ በመስፋፋት ላይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 16 ሞዴል መንደሮች በ16 ወረዳዎች ተገንብተዋል።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ኢኒሺዬቲቩ የአርሶ አደር ኑሮ ዘዬን ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ጋር ለማቆራኘት ያስቻለ ነው። የተሻለ መኖሪያ ቤት ኖሮት በጓሮው የሚበላ ነገር ካጣ ሕይወቱ ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም። ይህም በመሆኑ ቤቶቹን ከእያንዳንዱ የግብርና ልማት ዘርፎች ጋር በማጣመር እንዲገነቡ የተደረገው። ይህም የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ስትራቴጂን የሚያጠናክርና ገበያን የማረጋጋት ዓላማን የያዘ ጭምር ነው። በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ የተገኘው መልካም ውጤት በቀጣይ በሁሉም ወረዳዎች የሚስፋፋ ሲሆን በዞን እና ወረዳ መዋቅሮች ድጋፍና ክትትል በቀበሌ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አንስተዋል። ይህ ኢኒሼቲቭ የሀገራዊ ብልጽግና ጉዞ አንዱ አቅም ነው። የተደመረ የማኅበረሰብ ብልጽግና ሀገርን ከፍ ያለ የዕድገት ማማ ላይ ያስቀምጣታል። እነሆ የክልሉ አርሶ አደሮች የአካባቢያቸውን ጸጋ ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ የሚቀይሩበት መስክ በሞዴል መንደር ምክንያት እጃቸው ላይ ደርሷል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉትም በብዙ መንገድ ጨለማ የከበበው የገጠሩ ማኅበረሰብ ሕይወት ዛሬ ብርሃን ማየት ጀምሯል። ይህ የብርሃን ፋና እየተቀጣጠለ ወደ ብዙኃኑ ሊደርስ የሁሉንም ፍላጎት አነሳስቷል። ሥሩ ከማለት ይልቅ ሠርቶ ማሳየትን የሚያስቀድመው የመደመር መንግስት የፈጠራቸው የገጠር ሞዴል መንደሮች ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን በዘላቂነት የሚያሳምሩ ናቸው። ሰላም እንሰንብት!  
ትንታኔዎች
የግብጽ እኩይ ሴራ የማይገታው የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት መብት
Aug 19, 2026 768
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች የምትገኘው እና የቀጣናው የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋት ዋና መሠረት ነች። የኢትዮጵያ፣ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የፖለቲካ ፍላጎት ሳይሆን ሀገራዊ ሕልውናንና ደህንነትን የማረጋገጥ፣ የልማትና ብልጽግናን ዕውን የማድረግ የትውልድ ጥያቄ ነው። ትልቅ አቅም ያላት ኢትዮጵያ በመልክዐ-ምድራዊ እስር ውስጥ እንድትቀር የሚደረገው ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍትሕን የሚቃረን አካሄድን ለማረም ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት የነበራት የባህር በር ባለቤትነት እና የማሪታይም መብት በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እየሰራች ነው። ይህ የኢትዮጵያ ፍትሐዊና የማይቀረው የሕልውና ጥያቄ በዓለም አቀፉ የባሕር ሕግ ኮንቬንሽን (UNCLOS) የተረጋገጠ እና በጋራ ተጠቃሚነት (Win-Win) መርሕ ላይ የተመሠረተ ቢሆንም፣ የግብጽ ፖሊሲ አውጪዎች ግን ይህንን የሕልውና ጥያቄ ለማክሸፍ የሴራ እና የከበባ ስትራቴጂያቸውን ለማስፈጸም እየሰሩ ይገኛሉ። የግብጽ ሴራ በዋናነት ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ለወደብ ኪራይ እንድታወጣ በማስገደድ፣ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት የሚወጣው ካፒታል እንዲሟጠጥ በማድረግ የሀገሪቱን የኢንዱስትሪያላይዜሽንና የልማት ዕድገት ለማቀጨጭ ያለመ የኢኮኖሚ ዘመቻ ነው። በተጨማሪም ግብጽ የቀይ ባሕርን ማሪታይም ቀጣና “የባሕር ዳርቻ ሀገራት ብቻ (Littoral States) ይዞታ" አድርጋ በመሳል፣ የኢትዮጵያን ታሪካዊና ሕጋዊ የመጠቀም መብት በመካድ ከማንኛውም የቀይ ባሕር የደህንነትና የኢኮኖሚ ስብስብ እንድትገለል እየሰራች ትገኛለች። ግብጽ ከኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርጋቸው ወታደራዊ ስምምነቶች በሰሜንና በምሥራቅ ድንበሮች አካባቢ አዲስ የደህንነት ስጋት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያ ሀብቷንና ትኩረቷን ወደ የብስ ጥበቃ እንድታዞርና ለባህር ኃይል ግንባታ የምታውለውን አቅም እንድታበታትን የታለመ የከበባ ስልትም ነው። በዓለም አቀፍ የፋይናንስና የኢንቨስትመንት ተቋማት ዘንድ የምታደርገው የዲፕሎማሲ ጫና፣ ኢትዮጵያ ለወደብ እና ለትራንስፖርት ኮሪደሮች ልማት የሚሆን የውጭ ኢንቨስትመንት እንዳታገኝ እና የቀይ ባሕር አካባቢ የስጋት ቀጠና ተደርጎ እንዲቆጠር በማድረግ ኢንቨስተሮች እንዲሸሹ በማድረግ ላይ ናት። በጎረቤት ሀገራት ዘንድ የጥርጣሬ እና የስጋት ግንብ በመገንባት፣ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር የምታደርጋቸው ፍትሐዊና የጋራ ዕድገትን ያለሙ የወደብ ስምምነቶች የሉዓላዊነት መጣስ ተደርገው እንዲቆጠሩ የማስፈራራትና የሐሰት ትረካና ዘመቻ ታካሂዳለች። ግብጽ የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት ላይ አንድ ወጥ አቋም እንዳይዙ ለማድረግ ድርጅቶቹን የፖለቲካ ፍልሚያ መድረክ በማድረግ የቀጣናውን ተቋማዊ ትብብር የማደናቀፍ ተግባር እያከናወነች ይገኛል። የግብጽ ሚዲያዎች የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ የ130 ሚሊዮን ሕዝብ የረጅም ጊዜ ሕልውና እና የትውልድ ጥያቄ መሆኑ እየታወቀ ጠባብ የፖለቲካ አጀንዳ በማስመሰል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲይዝ የማድረግ ስራ ላይ ተጠምደዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና (AfCFTA) ውስጥ የምታደርገውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ፣ የወደብ ትራንዚት ወጪዋ ከፍተኛ ሆኖ እንዲቀጥል በማድረግ ምርቶቿ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ጫና ለመፍጠር ትሰራለች። የግብጽ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን ለዘለቄታው የመልክዐ-ምድር እስረኛ አድርጎ በማስቀረት፣ በምሥራቅ አፍሪካ የሚኖራትን ጂኦ-ፖለቲካዊና የኢኮኖሚ የበላይነት መግታት ነው። ሆኖም የግብጽ ሴራ የኢትዮጵያን የልማት መንገድ ሊያስቆመው አይችልም። ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በሕዝቦቿ የማይበገር ጽናትና ቁርጠኝነት እውን እንደሆነ ሁሉ፤ በቀይ ባህር ላይ ህጋዊና ፍትሃዊ መብትን የማረጋገጥ ጉዞም የቀጣናውን የታሪክ ሂደት የሚቀይር የማይቀለበስ ብሔራዊ የህልውና ጉዳይ ነው።
መደመር የደረመሠው የጠላት ካምፕና የባንዳዎች እሪታ
Aug 19, 2026 575
በምስራቅ አፍሪካና በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የካይሮ እጅ ሁልጊዜም ኢትዮጵያን ማዕከል ያደረጉ እኩይ ስትራቴጂዎችን በመተለም ይታወቃል። የዓባይ ወንዝ ዋነኛ ምንጭና የተፈጥሮ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያን ማዳከም፣ የውስጥ ግጭቶችን ማበረታት እና በቀይ ባሕር እንዲሁም በኤደን ባሕረ-ሰላጤ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍላጎት ማደናቀፍ የግብፅ የረጅም ጊዜ የውጭ ፖሊሲ መሠረት ሆኖ ቆይቷል። ግብፅ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በወታደራዊ ኃይል ኢትዮጵያን በግልጽ ወርራ ለመቆጣጠር ባደረገችው ሙከራ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1875 በጉንደት እንዲሁም 1876 በጉራዕ ጦርነቶች በኢትዮጵያ አሳፋሪ ሽንፈት አስተናግዳለች ። ከዚህ የቀጥታ ወታደራዊ ሽንፈት በኋላ ካይሮ ኢትዮጵያን በግልጽ ጦርነት ማንበርከክ እንደማትችል ተረድታ ወደ ተዘዋዋሪ የውስጥ ሴራና የእጅ-አዙር ጦርነት ተሸጋግራለች። ካይሮ ኢትዮጵያ ጠንካራና የበለፀገች ሀገር ሆና ከተነሳች በዓባይ ውሃ ላይ ያላትን አጠቃላይ የበላይነት እንደምታጣ ስለሚሰማት፣ የሀገሪቱን እድገት የማደናቀፍና በጂኦፖለቲካው መስክ ወደብ አልባ አድርጎ የመዝጋት ስትራቴጂን ለዘመናት ስትከተል ኖራለች። ይህም የታሪክ እውነታ ከትላንት እስከ ዛሬ በስውርና በግልጽ የሴራ መረቦች ተሸርቦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሲፈታተን የኖረ መራራ እውነት ነው። የቡትሮስ ብትሮስ ጋሊ የዲፕሎማሲ ሽፋን እና ኢትዮጵያን ወደብ የማሳጣት ሴራ በታሪክ አጋጣሚዎች እንደምናየው፣ በግብፅ የፖለቲካ ልሂቃን የታቀዱ ሴራዎች በዓለም አቀፍ መድረኮች እንዴት ተግባራዊ እንደሆኑ አንደኛው ማሳያ የቀድሞው ግብፃዊ ዲፕሎማት ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ አካሄድ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በ1970ዎቹ መጨረሻ በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራር በነበሩበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ በውስጥ ግጭት እንድትታመስና የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ ስጋት እንዳትሆን ከበስተጀርባ የዓመፅ ኃይሎችን የማጠናከር ስራ ሲሰሩ እንደነበር የሚታወቅ ሃቅ ነው። ቡትሮስ-ጋሊ በውሃ ፖለቲካ ረገድ በሰጡት የታወቀ ንግግራቸው “ቀጣዩ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና የሚካሄደው ጦርነት በፖለቲካ ምክንያት ሳይሆን በውሃ ምክንያት የሚደረግ ይሆናል” በማለት ለቀጣናው ያሰቡ መስለው የካይሮን የውሃ የበላይነት ስጋትና ፍላጎት በግልጽ አንጸባርቀው ነበር። ይህ ንግግራቸው ግብፅ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት የመቆጣጠር ፍላጎቷንና ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ የልማት ፕሮጀክቶችን እንዳታካሂድ ለማድረግ የምታደርገው ሴራ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲያገኝ ዓላማ ያደረገ አደገኛ ንግግር ነው። በኋላም እ.ኤ.አ በ1993 ኤርትራን ከኢትዮጵያ በመገንጠል ሂደት ውስጥ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የስድስተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ ነበሩ። በወቅቱ 99 ነጥብ 8% የሚሆኑት ኤርትራዊያን በሕዝበ ውሳኔ ነጻ ሀገርንትን መርጠዋል በሚል ሕወሃትና ሻዕቢያ የሰሩት ድራማ ተቀባይነት አንዲያገኝ የተመድ ዋና ጸሐፊው ከፍተኛ ሴራ ሰርተዋል። ይህ የኤርትራ ህዝብን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በሻዕቢያ ባርነትና ግዞት እንዲማቅቅ ያደረገው የሕዝበ ውሳኔ ድራማ ላይ ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊ የመሪ ተዋናይነትን ሚና ተጫውተዋል። በሂደቱም ዋነኛ ዓላማቸው የሆነውን ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በሯን እንድታጣ አድርገዋል። ይህም የካይሮ የረጅም ጊዜ “ኢትዮጵያን የመዝጋት” ስትራቴጂ አካል እንደነበር ግልጽ ነው። የካይሮ መጥረቢያ እና አሁናዊው የጥፋት መንገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት የመጥረቢያ ተምሳሌታዊ ማብራሪያ፣ ሕገ ወጡ ሕወሃትን እንደ መጥረቢያ ብረት፤ ሻዕቢያን ደግሞ እንደ መጥረቢያ ዛቢያ ያስቀመጡ ሲሆን፤ መጥረቢያውን የሚያዘውና የሚወረውረው ሌላ ሶስተኛ አካል መኖሩንም ተናግረዋል። እንደሚታወቀው መጥረቢያ አንድን ነገር የመቁረጥና የማፍረስ ስራ ለማከናወን የሶስት አካላት ቅንጅት ያስፈልገዋል፦ ወርዋሪው (እጁ)፣ ዛቢያው (መያዣው) እና ብረቱ (ቁራጩ)። በዚህ ተምሳሌት ውስጥ ወርዋሪው ወይም መጥረቢያውን ጨብጦ ስራ ላይ የሚያውለው አካል ግብፅ ናት። ወርዋሪው ሁልጊዜም ከበስተጀርባ ሆኖ ስትራቴጂ ይነድፋል፣ ፋይናንስና ወታደራዊ ድጋፍ ያቀርባል፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሽፋን ይሰጣል። በሌላ በኩል የመጥረቢያ ብረት ያለ ዛቢያው (መያዣው) ኃይል አግኝቶ ማረፍ አይችልም፤ ዛቢያውም ያለ ወርዋሪው እጅ መንቀሳቀስ አይችልም። በዚህ ሂደት ሻዕቢያ (እንደ ዛቢያ) በቀጣናው ውስጥ የካይሮን ፍላጎት ለማስፈጸም የመያዣነት ሚና ይጫወታል። ቀጣናውን ለማተራመስ በሞመከር የካይሮን ስትራቴጂካዊ ፍላጎት ለማሳካት መንገድ ይከፍታል። ህገ-ወጡ ህወሓት ደግሞ እንደ መጥረቢያ ብረት በሀገር ውስጥ ሆኖ የሀገሪቱን መዋቅር፣ የህዝቦችን አንድነት እና ስትራቴጂካዊ ብሔራዊ ጥቅም ለመሸርሸር የሚሰራ ተላላኪ መሳሪያ ነው። በዚህ የሴራ ትስስር አሁን ላይ ኢትዮጵያ በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት ማደናቀፍ ዋነኛ ዓላማው አድርጎም እየሰራ ይገኛል። ግብፅ “የቀይ ባሕርና የኤደን ባሕረ-ሰላጤ የባሕር ወሰን ያላቸው ሀገራት ብቻ ናቸው በውሃው ላይ መወሰን ያለባቸው” የሚል መርህ በማንሳት፣ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትንና በቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኘውን ትልቁን ኢኮኖሚ (ኢትዮጵያን) ያገለለ ህገ-ወጥ ስብስብ ለመፍጠር እየሰራች ነው። በተጨማሪም በቅርቡ ከሶማሊያና ከሌሎች የአካባቢው ሀገራት ጋር የተደረጉ የውትድርናና የደህንነት ስምምነቶች፣ የሶማሊያን ሰላም ለማስጠበቅ ሳይሆን ቀጣናውን ለማተራመስና ወታደራዊ ስጋት ለመፍጠር የተቃኙ ናቸው። ይህ ሁሉ አካሄድ ዋነኛ ዓላማው ቀጣናውን የውክልና ጦርነት ማዕከል በማድረግና ኢትዮጵያ ወደ ባሕር እንዳትቀርብ ሆነ ተብሎ የተሰላ ሴራ ነው። ከቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ እስከ ዛሬው የቀይ ባሕር ሴራዎች ድረስ የተዘረጉት መረቦችም ይህንኑ እውነት ያሳያሉ። የካይሮ መጥረቢያዎችን ያዶለዶመው የመደመር መንግሥት ጥንካሬ ግብጽ እያከናወነችው ባለው አሁናዊ ሴራ ውስጥ የካይሮ ስትራቴጂስቶች የሳቱት ትልቅ እውነታ አለ። የግብጽ የሴራ መጥረቢያዎች ለመቁረጥ የሚሞክሩት በፈተናዎች የማትበገረውን እና እንደ ወርቅ በእሳት ውስጥ ተፈትና ያለፈችውን ኢትዮጵያን መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በታሪኳ የውጭ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎችን አሸንፎ መውጣት እንግዳ የሆነባት ሀገር አይደለችም። ባለፉት ክፍለ ዘመናት በወረራ፣ በውስጥ አለመረጋጋትና በጂኦፖለቲካዊ ከበባዎች ውስጥ አልፋ የጸናች ሀገር ናት። ወርቅ በእሳት ውስጥ ሲያልፍ ቆሻሻው ተወግዶ ይበልጥ እንደሚበራ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በተጋረጡባት የህልውና ፈተናዎች ሁሉ አልፋ ይበልጥ እየጠነከረችና እየተደራጀች መምጣቷ የታሪክ እውነታ ነው። አሁን ባለንበት ዘመን ደግሞ ይህ ጥንካሬዋ ይበልጥ ጎልብቷል። የመደመር መንግሥት ቁልፍ ፍልስፍና እና እየተገበራቸው ያሉ እርምጃዎች የካይሮን የረጅም ጊዜ የእጅ አዙር ጦርነትና ሴራዎችን ከንቱ ያደረገ ነው። የመደመር መንግሥት የውጭ ጫናዎችንና ሴራዎችን ለመመከት የመጀመሪያው ምሽግ የውስጥ አቅምን ማጠናከር መሆኑን በመገንዘብ፣ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለፍፃሜ ማብቃትና ግዙፍ የግብርና፣ የአረንጓዴ አሻራ እና የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን እውን አድርጓል። ይህም ግብፅ ኢትዮጵያን በልማት እንዳትበለፅግ ለማድረግ ያቀደችውን ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ አክሽፎታል። ካይሮ ኢትዮጵያን በጂኦፖለቲካዊ ከበባ ለማዳከምና በውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የነደፈችው የረጅም ጊዜ የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት ባስመዘገባቸው የልማትና የዲፕሎማሲ ድሎች ምክንያት ሙሉ በሙሉ ተደርምሷል። ይህ የጠላት ካምፕ መደርመስና የኪሳራ ስሌት ደግሞ በካይሮ ስትራቴጂስቶችና በውስጥ ተላላኪዎቻቸው (ባንዳዎች) ዘንድ ታላቅ ድንጋጤንና ተስፋ የመቁረጥ እሪታን ፈጥሯል። በመሆኑም የተበተነው የጠላት ካምፕና የተበሳጩት ባንዳዎች ብቸኛ አማራጭ አድርገው የያዙት በሳይበርና በሚዲያ ምህዳር የሃሰት መረጃዎችን ማንደድና የፕሮፓጋንዳ ማዕበል መፍጠር ቢሆንም፣ ይህም የተስፋ መቁረጥ ድምፅ ብክለት እንጂ የኢትዮጵያን የጽናት ጉዞ የሚያስተጓጉል አይሆንም። በሌላ በኩል ግብፅ “የቀይ ባሕር ሀገራት ጥምረት” በሚል ስም ቀጣናውን ለማተራመስና እርስ በርስ ጥርጣሬ ለመፍጠር የምታደርገውን የሴራ መረብ፣ የመደመር መንግሥት የጋራ እድገትና የጋራ ተጠቃሚነት መርህን በማስቀደም በዲፕሎማሲው መስክ እየመከተው ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ ምክክር የጋራ ጉዳዮቻቸው ላይ በጋራ እንዲወስኑ በማድርግም የካይሮ ስትራቴጂስቶች በኢትዮጵያ የውስጥ ልዩነቶች ላይ እሳት በማንደድ ሀገሪቱን ለማፍረስ የጠነሰሱትን ሴራ ከንቱ አድርጎታል። በአጠቃላይ ታሪክ እንደሚነግረንና የወቅቱ እውነታ እንደሚመሰክረው፣ የግብፅ የሴራ መጥረቢያዎች በፈተናዎች እሳት ተፈትና ባላለፈች ደካማ ሀገር ላይ ያረፉ አይደሉም። ለመቁረጥ የሞከሩት በጽናት፣ በህዝቦቿ መስዋዕትነትና በፅኑ ታሪካዊ መሰረት ላይ የቆመችውን ኢትዮጵያን ነው። አሁን ላይ በመደመር መንግሥት መሪነት እየተገነባ ያለው የውስጥ አቅም፣ የልማት ስኬትና በራስ መተማመን የካይሮን የረጅም ጊዜ የከበባ ሴራ ሙሉ በሙሉ ወድቅ ማድረጉን ቀጥሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ሁሉ አሸንፎ ማለፍ የሰርክ ተግባሯ እንደመሆኑ መጠን፣ የዛሬውንም የጂኦፖለቲካ ውጥረትና የሴራ መረብ በጽናት አልፋ የቀጣናው የልማትና የሰላም ማዕከል ሆና መቀጠሏ የማይቀየር እውነት ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ፦ የምግብ ሉዓላዊነት ምሰሶ
Aug 14, 2026 413
(በሙሴ መለሰ) የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአፈር መሸርሸር እና የተፈጥሮ ሀብቶች መመናመን በአሁኑ ወቅት የዓለማችን ዋነኛ የህልውና ስጋቶች ሆነዋል። ኢትዮጵያም የዚህ ችግር ተጠቂ ናት። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ ተግዳሮቶቹን በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ነው። የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም፣ የደን ሽፋንን መጨመር፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት በወቅቱ አረንጓዴ ዐሻራ ሲጀመር የነበሩ አበይት አላማዎች ናቸው። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ መጀመሩ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘንድሮው ዓመት ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ መቀመጡን እና በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የምታስተናግደው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ድረስ የሀገሪቱን ግብ ወደ 65 ቢሊዮን ከፍ ለማድረግ መታቀዱን ገልጸዋል። ሐምሌ 27/ 2018 በተካሔደው የዘንድሮው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይም 800 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል ታቅዶ፣ 805 ነጥብ3 ሚሊዮን በመትከል ከእቅዱ በላይ ማሳካት ተችሏል። ከ26 ነጥብ2 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው የተሳተፉበት ይሄ መርሃ-ግብር በአጠቃላይ 294 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ነበር። በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ለመትከል ከታቀደው ስምንት ቢሊዮን ችግኞች መካከልም ከ6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ መተከሉን መረጃዎች ያሳያሉ። የአረንጓዴ ዐሻራ ከአካባቢ ጥበቃ ስራ ባሻገር ሀገራዊ የምግብ ዋስትናን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። መርሃ-ግብሩ ከተራቆቱ መሬቶች መልሶ ማገገም ባለፈ፣ በምግብ ራስን ለመቻል እየተደረገ ባለው ጥረት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ ዐሻራ ከተለመደው የደን ልማት በተለየ መልኩ የግብርና ደንን (Agro-forestry) በማስፋፋት የአርሶ አደሩንና የከተማውን ማህበረሰብ የምግብ ፍላጎት በቀጥታ መመለስ ላይም ያተኮረ ነው። እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን፣ ቡና እና ሙዝ ያሉ የምግብና የፍራፍሬ ችግኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ ተተክለዋል። ይህ አካሄድ አርሶ አደሮች ከሰብል ምርት በተጨማሪ ከተተከሉት ዛፎች የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። ከዛም ባለፈ ለገበያ በማቅረብ የሚገኘው ተጨማሪ ገቢም የአርሶ አደሩን አቅም አሳድጎታል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮ አካባቢ ምህዳርን ለመጠበቅ የሚያስችሉ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል። የተተከሉት ችግኞችም ትርጉም ያላቸው የዜጎችን ተጠቃሚነትና የአካባቢ ጥበቃን ታሳቢ ያደረጉ ናቸው። ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚሆነው የጥምር እርሻ ደን ሲሆን 35 በመቶ የሚሆነው ደግሞ የደን ዛፍ ነው። ቀሪው ደግሞ የከተማ ውበት ዛፎች ናቸው። የተተከሉ ዛፎች አፈርን ከውሃ መሸርሸር በመጠበቅና የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጨምር በማድረግ የሰብል ምርታማነትን ያሳድጋሉ፤ እንዲሁም የደረቁ ምንጮችን በማነቃቃት የመስኖ ልማትን ያበረታታሉ። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተከላው ሂደት፣ የንብ እርባታንና የእንስሳት መኖ አቅርቦትን በማሳደግ የዘላቂ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል። በሌላ በኩል፣ ይህ አገራዊ ንቅናቄ በከተማ ግብርና ላይ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በከተሞች ዙሪያ የሚለሙ የፍራፍሬ ችግኞች በአነስተኛ ይዞታዎች ላይ የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ናቸው። ይህ አካሄድ በከተሞች የሚታየውን የምግብ ፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን በመቅረፍ፣ በምግብ ራስን ከመቻል አንጻር የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የሚያደርግ ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገሪቱን የምግብ ዋስትና በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት እና በምግብ ራስን የመቻል አገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚተገበር ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ነው። ንቅናቄው ከተራቆቱ መሬቶች መልሶ ማገገም ባለፈ፣ በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት የሚያፋጥንበትን ሁለንተናዊ አቅም ፈጥሯል። ኢትዮጵያዊያን እንደ አድዋ እና እንደ ህዳሴ ግድብ ሁሉ በአንድ ድምጽ በመደመር እሳቤ በአንድነት ተነስተው በጋራ እየፈጸሙት ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከችግኝ መትከልም በላይ ነው። ይሄ አንድነት ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ የተላቀቀች ለቀጣናው ለአህጉሩና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በአርዓያነት እያስጠቀሳት የሚገኝ ነው። ትውልዱ በየዓመቱ በሚከናወነው በዚህ መርሃ-ግብር ዐሻራውን ከማሳረፍ ባለፈ በእንክብካቤውም የተናበበ ሆኖ መቀጠል የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን የማድረግ መሻቱን ማሳካት ይጠበቅበታል።
ከአረንጓዴ አሻራ እስከ ዓለም ገበያ - የኢትዮጵያ ቡና ልማት አዲስ የዕድገት ምዕራፍ
Aug 13, 2026 549
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቡና መገኛ ከመሆኗም ባለፈ ምርቱ አሁንም ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብትና ማህበራዊ ህይወት ትልቅ መሰረት ያለው ነው። የዓለም የቡና ዝርያዎች ሁሉ መገኛ የሆነው የአረቢካ ቡና ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘውም በኢትዮጵያ እንደሆነ ይታወቃል። በኢትዮጵያ ቡና መጠጣት የዕለት ተዕለት ባህል ሲሆን፣ የቡና አፈላል ስነ ስርዓት ሰላምን፣ አንድነትንና ማህበራዊ ውይይትን የሚያጠናክር ትልቅ እሴት ተደርጎም ይወሰዳል። በአሁኑ ወቅት ቡና ለሀገሪቱ ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኝ ቀዳሚው የግብርና ምርት በመሆን ማዕከላዊ የኢኮኖሚ ሚናውን እየተጫወተ ይገኛል። አብዛኛው የኢትዮጵያ ቡና የሚመረተው በተፈጥሯዊ መንገድ በገበሬዎች ማሳ ላይ ወይም በዱር ውስጥ በመሆኑ፣ ለሰው ሰራሽ ማዳበሪያና ኬሚካል ተጋላጭ አይደለም። ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተመራጭነት ይበልጥ ከፍ አድርጎታል። ከኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ምሰሶ አንዱ የሆነው ቡናችን ለሀገሪቷ እያስገኘ ያለው ገቢም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ካነሷቸው ጉዳዮች መካከልም አንዱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዋልታ የሆነው ቡና ነበር። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከብራዚልና ኮሎምቢያ በመቀጠል በዓለም 3ኛዋ ትልቋ የቡና ላኪ ሀገር መሆኗን እና በአፍሪካም ቀዳሚ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጸዋል። በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ከቡና ወጪ ንግድ 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን፣ ይህ ውጤት ባለፉት 17 ዓመታት በድምሩ ከተገኘው 3 ነጥብ3 ቢሊዮን ዶላር ጋር ሲነጻጸር በዘርፉ የተመዘገበውን ከፍተኛ ዕድገት ያሳያል ብለዋል። ለተመዘገበው ውጤት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም አጠናክራ መጠቀም እንዳለባት ተናግረዋል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ የኢትዮጵያን የቡና ዘርፍ ከዘልማዳዊ አሰራር ወደ ዘመናዊ ምርታማነት ለማሸጋገር የሚያስችል አዲስ የ10 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ እና የተሻሻለ የልማት ፓኬጅ መዘጋጀቱን በቅርቡ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል። ቡና በሀገሪቱ ኢኮኖሚ፣ የሚሊዮን አርሶ አደሮች የኑሮ መሠረትና የወጪ ንግድ ዋነኛ ምሰሶ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ታላቅ ሀብት በጥራትና በዘላቂነት በማሳደግ ከምርት ወደ እሴት፣ ከእሴት ወደ ዓለም ገበያ ማሸጋገር የዘርፉ ዋነኛ አቅጣጫ መሆኑን ተናግረዋል። ይህንኑ ስትራቴጂ ለማሳካት የተጀመረው ሃገራዊ የቡና ምርትና ምርታማነት ኢኒሼቲቭ በአሁኑ ወቅት በሔክታር 9 ኩንታል የሆነውን የቡና ምርታማነት ወደ 21 ኩንታል ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ሚኒስትሩ አብራርተዋል። በተጨማሪም በ 1 ነጥብ15 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ላይ የቡና ልማት ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን፣ ለዚህም ምርጥ የቡና ዘር አጠቃቀም፣ የተቀናጀ የአፈር ንጥረ-ነገር፣ የቡና ተክል ጥግግት፣ የገረዛና የጥላ ዛፍ አያያዝ፣ የተቀናጀ የተባይ መከላከል፣ የመስኖ፣ የማዳበሪያ እንዲሁም የተሻሻለ የምርት አሰባሰብና የዕድሳት ሥራዎችን ያካተቱ ዘጠኝ የትኩረት መስኮች ተለይተው ወደ ሥራ መግባታቸውን አመልክተዋል። ይህ አዲሱ የቡና ልማት ኢኒሼቲቭ አርሶ አደሮችን፣ የማህበራትንና የባለሙያዎችን ግንዛቤና አቅም ለማሳደግ ሰፊ የንቅናቄ ሥራዎችን እንደሚከናውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በቡና ወጪ ንግድ ከአፍሪካ ቀዳሚና ከዓለም 3ኛዋ ትልቅ ላኪ ሀገር በመሆን ያሳየችው እመርታ፣ የዘርፉን ታላቅ የምጣኔ-ሀብት አቅም በተጨባጭ የሚያሳይ ነው። ለዚህ ደግሞ ላለፉት ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ምህዳር በማስተካከል ረገድ የራሱን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ይታወቃል። በዚህም መርሃ-ግብሩ በተጀመረበት 2011 ዓ.ም 600 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የተተከለው የቡና ችግኝ በየዓመቱ እያደገ በመሔድ በ2017 ዓ.ም ላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሸፈን ተችሏል። ይሄ በመሆኑም የቡና ምርታማነት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል። በ2011 ዓ.ም. ግማሽ ሚሊዮን ቶን የነበረው ዓመታዊ የቡና ምርት 2017 ዓም ላይ ወደ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ምርት ማግኘት በመቻሉ ኢኮኖሚው ላይ ያለውን ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ማስቀጠል ችሏል። በመሆኑም፣ የተያዘውን የተቀናጀ የልማት ስትራቴጂ በተግባር በመተርጎም የቡናን ምርት በጥራትና በብዛት ማሳደግ፣ የሀገሪቱን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት ከመደገፍ ባለፈ የኢትዮጵያን ቡና የወደፊት ጉዞ እና ዓለም አቀፋዊ መሪነት እጅግ አስተማማኝ ያደርገዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 12043
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 21778
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14810
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20554
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 104551
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79475
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57839
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55434
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 39691
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 39553
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 39030
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 37578
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 104551
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79475
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57839
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55434
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የአረቡ ዓለም ከግብፅ ምን አተረፈ?
Aug 19, 2026 329
የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ አካሄድ በታሪካዊ እውነታዎች እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ላይ እየተመሠረተ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ ጊዜ ያለፈባቸው የጂኦ ፖለቲካዊ የመጠላለፍ አካሄዶች ዋጋ ቢስነትና ጥቅም አልባነት በግልጽ እየታየ ይገኛል። ለብዙ አስርት ዓመታት ግብፅ የዓረብ ሊግን ለራሷ ጠባብ ፍላጎቶች እና ጂኦፖለቲካዊ አጀንዳዎች ማስፈጸሚያነት በሰፊው ስትጠቀምበት ቆይታለች። ሆኖም ይህ ጥቅምና ጉዳትን ብቻ መሰረት ያደረገ ግንኙነት አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ያስነሳል፦ ለመሆኑ የዓረቡ ዓለም ከግብፅ በምላሹ ያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? ለዚህ ጥያቄ አጭሩ መልስ ምንም የሚል ነው ሲል “What Has the Arab World Gained from Egypt? Why Ethiopia Belongs in the Arab League?” ፀሐፊው እና በፖለቲካና ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ በቋሚነት የሚተነትነው አስተያየት የሚሰጠው ጅብሪል ላሞ በኢዜአ እንግሊዘኛ ገጽ ባሳፈረው ሐተታ ላይ ፣ የግብጽ ፖሊሲዎች እንዲሁም ለሁለት አስርት ዓመታት የዘለቀው አምባገነናዊ አስተዳደር የጋራ ጥንካሬን ከመፍጠር ይልቅ የቀጣናውን አለመረጋጋት ማባባሳቸውን ገልጿል። እነዚህ ፖሊሲዎች፣ በምሥራቅ አፍሪካ እና በቀይ ባሕር አካባቢም ውጥረትን እያባባሱ እንደሚገኙ አመልክቷል። እነዚህ አካባቢዎች ለዓረቡ ዓለም የራቁ አይደሉም፤ ይልቁንም ለዓረቡ ዓለም ደኅንነት፣ የባሕር ንግድ፣ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የምግብ ዋስትና እጅግ ወሳኝ እና ስትራቴጂካዊ ማዕከላት ናቸው። የግብፅ ከፋፋይ ቀጣናዊ አካሄድ ከታዩባቸው ጉልህ ማሳያዎች አንዱ በኤርትራ ጉዳይ እና በሰፊው የኢትዮጵያ ግዛት አንድነት ላይ የነበራት ታሪካዊ ጣልቃ ገብነት ነው። ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ቀጣናዊ ተፅዕኖዋን ለመግታት በግብጽ ታስበው የተደራጁ ተገንጣይ ኃይሎችን እና ፖለቲካዊ ፕሮጀክቶችን በግልጽ ትደግፍ እንደነበረ ፀሐፊው አውስቷል። ከኢትዮጵያ የኤርትራ መገንጠል በምሥራቅ አፍሪካ ቀውስ የተሞላ ታሪክ ውስጥ አቢይ ክስተት ሲሆን፣ የውጭ ጂኦፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነቶች የሀገራትን እጣ ፈንታ እንዴት እንደሚያናጉ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የዲፕሎማሲ ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ የቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ እና የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ፣ ኢትዮጵያን ለማዳከም ታስቦ የተዘረጋውን የኤርትራን የመገንጠል ፕሮጀክት በመደገፍና በማፋጠን ረገድ ትልቅ ሚና ነበራቸው። በተጨማሪም ግብጽ በደቡባዊ የቀይ ባህር ቀጣና የምታካሂደው ቀውስ የመፍጠር እንቅስቃሴ፣ ለዓለም አቀፍ የባህር ንግድና ለቀጣናው ደህንነት ቀጥተኛ ስጋት ደቅኗል። በባብ-ኤል-ማንደብ የባሕር ወሽመጥ አካባቢ ውጥረቶችን በመቀስቀስ እና ተላላኪ ታጣቂ ቡድኖችን በማንቀሳቀስ፣ ወሳኝ የሆኑ የባህር መተላለፊያዎችን የጂኦፖለቲካዊ ግጭት መድረክ አድርጋዋለች። ይህም ለጠቅላላው የዓረብ ዓለም የኢነርጂና የምግብ አቅርቦት መሰረት የሆነውን የደህንነት መዋቅር አደጋ ላይ ጥሎታል፤ ሲሉ ጅብሪል ላሞ ያብራራሉ። ጅብሪል ላሞ በጽሑፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ የግብፅ ግልጽ የራስ ወዳድነት እንቅስቃሴዎች ቀጣናዊ ውጥረትን የሚፈጥሩ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ መቀላቀል ግን ለዓረቡ ዓለም እጅግ ከፍተኛ ጥቅም የሚያስገኝ ለውጥ አምጪ ዕድል ይዞ ይመጣል። በመደመር ፍልስፍና አሳታፊ ማዕቀፍ ሥር፣ ኢትዮጵያ ከማግለል ፖሊሲ ይልቅ የዓረቡን ዓለም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማስተሳሰር የሚያስችል የላቀ የዲፕሎማሲ አቅም አላት። በዚህም የአፍሪካ ዋነኛ የዲፕሎማሲ ማዕከል እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ የባለብዙ ወገን ትብብሮችን በመቅረጽ ረገድ ያላትን የካበተ ልምድ ታካፍላለች። የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ የመቀላቀል ጥረት ጊዜያዊ የፖለቲካ ስሌት ሳይሆን፣ የተፈጥሮ የታሪክ ጥሪ ነው። ከ135 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ፣ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እና ጥልቅ የሥልጣኔ መሠረት ያላት ይህች የቀይ ባሕር ሀገር፣ አባልነቷ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ መካከል ስትራቴጂካዊ ድልድይ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር ያላት ቁርኝት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በጋራ ታሪክ፣ ባህል እና የደም ትስስር ላይ የተገነባ ነው። እንደ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሉ የትምህርት ተቋማት፣ የኢትዮጵያ ጥናቶች በታሪክ ደረጃ ከመካከለኛው እና ከቅርብ ምሥራቅ ታሪክ (Near Eastern Studies) ተመድቦ መጠናቱ፤ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ከቀጣናው ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ ውህደት የሚያረጋግጥ ሕያው ማሳያ ነው። የባብ-ኤል-ማንደብ የባህር ወሽመጥ በጭራሽ መሰናክል አልነበረም፤ ይልቁንም ንግድን፣ ባህልን እና ማህበረሰቦችን በቀይ ባሕር በኩል ያገናኘ ዋንኛ መተላለፊያ ሆኖ አገልግሏል። ከንጉሥ አብረሃ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ በኢትዮጵያውያን እና በመካከለኛው ምሥራቅ ሕዝቦች መካከል የጋራ የደም ትስስር እንደነበር የሚያረጋግጡ ዘመናዊ የስነ ህይወት( ጄኔቲክስ) ጥናቶች፣ የዚህን ታሪካዊ ቁርኝት እውነተኛነት በግልጽ ያሳያሉ። በቋንቋና በባህል ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት መሠረት ታሪካዊ ትስስር ያለው ነው። የሀገሪቱ የቋንቋና የሥነ-ጽሑፍ ውርስ ከዓረብኛ፣ አራማይክና ዕብራይስጥ ጋር በጽኑ የተሳሰረ ሲሆን፣ ይህም በምሥራቅ አፍሪካና በአረቢያ ልሳነ-ምድር መካከል ያለውን ጥልቅ የጋራ የሥልጣኔ ቁርኝት ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ አላት። የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ተስደው በንጉስ ነጃሺ ከለላ ማግኘታቸው የእስልምናን ህልውና የታደገ ታሪካዊ ክስተት ሲሆን፣ ይህም ሀገሪቱን ከዓረቡ ዓለም ጋር በጽኑ አስተሳስሯታል። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ የዓረብ ሊግን በኢትዮጵያ ላይ እንደ ተቋማዊ ተፅዕኖ ማሳደሪያ መሣሪያ ግብጽ ስትጠቀምበት ቆይታለች። ግብፅ የውጭ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ዕድገት፣ የህዳሴውን ግድብም ሆነ የባሕር በር ጥያቄን እንደ ሥጋት በሚያይ ጊዜ ያለፈበት ስሌት ላይ የተመሠረተ ነው። ግብፅ የራሷን የውሃ አቋም በሊጉ ላይ በመጫን፣ ተቋሙ ከኢትዮጵያ ጋር አላስፈላጊ ውጥረት ውስጥ እንዲገባ አድርጋለች። ጅብሪል ላሞ እንዳመለከተው፣ ከግብጽ የአግላይነት ፖሊሲ ይልቅ የዘመኑ ነባራዊ ሁኔታዎች ሙሉ ትብብርን የሚጠይቁ ናቸው። በመደመር መርህ፣ ኢትዮጵያ ለዓረቡ ዓለም ለዘመናት ከቆዩ የጥላቻ መንገዶች በላቀ ሁኔታ የተሻሉ ጥቅሞችን ማቅረብ ትችላለች። እያደገ የመጣው የኢንዱስትሪ እና የአረንጓዴ ኃይል አቅሟ፣ ኢትዮጵያን ለቀይ ባህር ቀጣና የመረጋጋት ምሰሶ አድርጓታል። የመካከለኛው ምሥራቅ ቀጣና የውሃ እጥረት እና የምግብ ዋስትና ሥጋት በተጋረጠበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ የውሃ ሀበት እና ለም መሬት ለቀጣናው ወሳኝ የግብርና-ኢንዱስትሪ አጋር ያደርጋታል። የዓረብ ሊግ አባል ሀገራት የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ብሔረተኝነት በመሻገር፣ የቀይ ባህርን ቀጣና የሥልጣኔ እውነታ መቀበል ይኖርባቸዋል። አረብ ሊግ እንደ ጅቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ኮሞሮስ እና ሞሪታኒያ አባል ሀገራት መያዙ፣ ስብስቡ የተለያዩ ቀጣናዊ እውነታዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑን ያሳያሉ። የዓረብ ሊግ ሙሉ አባልነት የኢትዮጵያን አፍሪካዊ ማንነት ሳይቀንሰው፣ አህጉሩን ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር የሚያገናኝ ዋነኛ ድልድይ የሚያደርጋት በመሆኑ፤ ሊጉ የኢትዮጵያን አጋርነት በመቀበል ለአዲስ አበባ ተገቢውንና ሕጋዊ ቦታዋን የሚሰጥበት ጊዜ አሁን እንደሆነ በመግለጽ ጅብሪል ላሞ ፅሁፉን ቋጭቷል።
በምክክር እንጂ በመሳሪያ ድምጽ ሀገር አይገነባም
Aug 8, 2026 758
ኢትዮጵያ የዛሬ ማንነቷና ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እዚህ እንድትደርስ በርካታ ውጣውረዶችን አልፋለች። በቀደመ ታሪኳም ዜጎች በራሳቸው የውስጥ ጉዳይ መስማማት ባለመቻል እርስ በእርስ ካደረጓቸው ግጭቶች ባለፈ የውጭ ሃይሎችም የራሳቸውን አሉታዊ ጫና ሲፈጥሩ ቆይተዋል፤ አሁንም ይህንኑ ለማስቀጠል ተላላኪዎቻቸውን ለመጠቀም ሲሞክሩ ይታያል። በአንድ ሃገር ውስጥ የማያግባቡ ጉዳዮች በየትኛውም አጋጣሚና የታሪክ ምዕራፍ ሊያጋጥሙ ይችላሉ። እነዚህን ችግሮች በሃይል ለመፍታት የሚደረገው የመሳሪያ ትንቅንቅ ግን አክሳሪና ዘመን እያለፈበትም ነው። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ሰላማዊ የእድገት ጉዞ ለማወክ የህዝቦቿን አንድነት ለመበጥበጥ ከቅርብም ሆነ ከሩቅ የሚመጡ ጠላቶች ጠፍተው አያውቁም። በየዘመናቱ የተሻገርናቸው የታሪክ ስብራቶችን ፣ የመብት ጥያቄዎችንና ሌሎችንም መነሻ በማድረግ በውስጥ ባንዳዎች እና በውጭ ባዳዎች አማካኝነት የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ለመክተት፣ የብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚደረጉ ሴራዎች ዛሬም ላይ ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት ተሰሚነትና ተጽዕኖ የሚያሳምማቸው ለዜጎቿን እኩል ተጠቃሚነትና ብልጽግና መረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚያስጨንቃቸው እነዚህ ሃይሎች በመብት ፣ በነጻነት፣ በዴሞክራሲ፣ በማንነትና በሌሎችም የሃሰት ትርክቶች መነሻነት በሩቅ ቢያቅታቸው በቅርብ የውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን እያደራጁ በጀት መድበው የጦር መሳሪያ አቅርበው ሀገር የማፍረስ ሙከራቸውን አላቋረጡም። በመደመር እሳቤ ሁሉንም በአንድ ላይ በማቀራረብና የጋራ ትርክቶችን በመገንባት ከልዩነት ይልቅ የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ዘላቂ ልማቷን መፃኢ ብሩህ ተስፋዋን ለማለምለም በሁሉም ዘርፍ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ተሳትፎ እየሰራች መሆኗም ምቾት ነስቷቸዋል። በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሔደ ያለውና ወርቃማው እድል ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ፣ የሚያስችሉ ወሳኝ ምዕራፎች ላይ ደርሷል ። በዚህ የምክክር ሒደት በሀገሪቱ የትኛውም ጥግ ያለ ዜጋ እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የተወከሉበት ፣ የብሔር፣ የፖለቲካ አመለካከትና የሃይማኖት ልዩነት የማያደናቅፉት ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እየተካሔደ ይገኛል። ጥያቄያችንን በጠብመንጃ አፈሙዝ እንፈታለን ያሉ ታጣቂዎችም ብረት በማስቀመጥ አጀንዳዎቻቸውን ይዘው ወደ ጠረጴዛው ቀርበዋል። ልክ ናቸው ሀገር ከሁሉም ነገር ትበልጣለችና ይሄንን ወርቃማ እድል ለመጠቀም ማሰብ ትክክለኛው ውሳኔ ነው። በትጥቅ ትግል ጥያቄያችንን እንመልሳለን በሚል ሽፋን የሌሎችን አጀንዳ ለማሳካት የሚደረግ ጥረት የሃገርና የትውልድ ጠባሳ ከማስቀመጥና የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው መገንዘብ ብልህነት ነው። የዚህ ምክክር ተሳታፊ/ተመካካሪ ከሆኑት የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) አመራር ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በዚህ ይስማማሉ ። ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ተስፋ የጣልንበት፣ በንግግር፣ በምክክር ሀገራችንን የምናስቀጥልበት፣ ሁሉም ተነጋግሮ ተመካክሮ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ከችግሮች ነፃ የሚያደርግበት ነው ይላሉ። ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚነጋገርበት፣ የሚመካከርበት እና በሃሳብ የበላይነት ጠንካራ ሃገር የሚፈጠርበት መልካም የታሪክ አጋጣሚ መሆኑንም ይናገራሉ። በምክክር፣ በድርድር የሕዝብን ጥያቄ በመመለስ ሀገርን የምናስቀጥልበትና የውጭ ኃይሎችን ጣልቃ ገብነት የምናስወግድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ነው ብለዋል። የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራር የቀድሞ ታጣቂ ጃል ሰኚም ይሄንኑ ሃሳብ ይጋራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ለዓመታት የቆዩ ልዩነቶችን ለመፍታት ሀገራዊ ምክክር መዘጋጀቱ ትልቅ እርምጃ እንደመሆኑ እሳቸውም ያላቸውን ሀሳብ በማንጸባረቅ እየመከሩ ይገኛሉ። እርሳቸውና ቡድናቸው ከዚህ ቀደም የትጥቅ ትግልን በመምረጥ ጫካ ገብተው እንደነበር አስታውሰው፤ ችግሮችን በመሳሪያ ከመፍታት ይልቅ በሰላማዊ የምክክር መድረክ መፍታት ጥሩ አማራጭ መሆኑን አምነው ወደ ሰላም መንገድ መምጣታቸውንም ተናግረዋል። ችግሮቻቸውን በምክክር የፈቱ ሀገራት በሁሉም ዘርፍ ዕድገታቸውን የሚያስቀጥሉ ሲሆኑ ወደ ትጥቅ ትግል ያመሩና ግጭት ውስጥ የገቡት ደግሞ በፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውድቀት ለከፋ ድህነት መዳረጋቸውን ጠቅሰዋል። የጦር መሣሪያ በመነቅነቅና ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ በመግባት የሚፈታ ችግር እንደሌለ የሚናገሩት ደግሞ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ(አብን) አመራሩ ተመካካሪ ጣሒር መሀመድ ናቸው። ጫካ ባለውና እዚህ ባለው ሰው መካከል ምንም ዐይነት የዜግነት ልዩነት እንደሌለ ገልጸው ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሃሳብ ለመታገል ልዩነቱን ለማቅረብ የፈለገ ሁሉም ዜጋ በምክክሩ የመሳተፍ ነጻነት እንዳለው ገልጸዋል። በሃገራዊ ምክክሩ ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሰላማዊ መድረክ መወያየት የተመረጠበት ዋና ምክንያት ዘላቂ ሰላም፣ አገራዊ መግባባት እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ ለማምጣት ነው:: የትጥቅ ትግል የዜጎችን ህይወት ያጠፋል፣ መሰረተ ልማቶችን ያወድማል፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድቀትንም ያመጣል: ፤ ሰላማዊ መድረክ ግን ያለምንም ደም መፋሰስ ሃሳብን በሃሳብ ለመሞገት እድል ይሰጣል:: በኃይል የሚመጣ ለውጥ ብዙውን ጊዜ አሸናፊና ተሸናፊን ስለሚፈጥር የቁስል እና የቂም ዑደትን ያስቀጥላል:: በሰላማዊ ውይይት የሚገኝ መፍትሄ ግን የሁሉንም ወገን ስጋት እና ፍላጎት ያገናዘበ በመሆኑ ዘላቂነት ይኖረዋል:: ሃገራዊ ምክክሩ የታጠቁ አካላትም ጭምር መሳሪያቸውን አስቀምጠው በሃሳብ እንዲፎካከሩ መንገድ ከፍቷል። ይህ ታሪካዊና ወርቃማ እድል ኢትዮጵያዊንን አግባብቶ ወደተረጋጋችና የበለጸገች ሃገር የሚመራ በመሆኑ ስኬታማነቱ አያጠራጥርም። ለእድለኛው ትውልድ ያጋጠመው ወርቃማው ስጦታ ሃገራዊ ምክክር የተቋቋመለትን ዓላማ ያሳካል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም