ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ፈረንሳይ ሞሮኮን በመርታት ለግማሽ ፍጻሜ አለፈች
Jul 9, 2026 305
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ማለፍ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በቦስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኪሊያን ምባፔ በ60ኛው እና ኡስማን ዴምቤሌ በ65ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ምባፔ በ28ኛው ደቂቃ ፍጹም ቅጣት ምት ስቷል። ፈረንሳይ በጨዋታው ፍጹም ብልጫ ወስዳለች። የተደራጀ መከላከል እና የመልሶ ማጥቃት የአጨዋወት ስልት የተከተለችው ሞሮኮ ግልጽ የግብ እድሎችን መፍጠር ተስኗታል። የ27 ዓመቱ ኪሊያን ምባፔ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ስምንት በማድረስ ከአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ ጋር በጎል እኩል በመሆን ሶስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል ብልጫ ወስዶ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ይገኛል። በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ 20 ጎሎች ከመረብ ላይ በማሳረፍ በምንጊዜም ከፍተኛ አስቆጣሪነቱ ከሜሲ (21 ጎል) በአንድ አንሶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ምባፔ በዓለም ዋንጫው የጥሎ ማለፍ ምዕራፍ 12ኛ ጎሉን በማስቆጠር በውድድሩ አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል። ለብሔራዊ ቡድኑ 64ኛ ጎሉን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ምባፔ በ77ኛው ደቂቃ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ ወጥቷል። የባለንዶር ባለቤቱ ኡስማን ዴምቤሌ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አምስተኛ ጎሉን አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ፈረንሳይ ግማሽ ፍጻሜውን የተቀላቀለች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች። በዓለም ዋንጫው ለግማሽ ፍጻሜ ስታልፍ የአሁኑ ለሰባተኛ ጊዜ ነው። ፈረንሳይ በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ሞሮኮ የዓለም ዋንጫ ጉዟዋ ሩብ ፍጻሜው ላይ አብቅቷል። ለተከታታይ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የመግባት ህልሟ ሳይሳካ ቀርቷል። በሩብ ፍጻሜው ላይ አፍሪካን የወከለችው ብቸኛ ሀገር ሞሮኮ ከውድድሩ ተሰናብታለች። የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር ከተሳተፉ 10 ቡድኖች መካከል የተሻለ ርቀት መጓዝ ችላለች። ሞሮኮ በ22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ የአፍሪካ ሀገር መሆኗ የሚታወስ ነው። በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ አፍሪካ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ 10 ሀገራት አሳትፋለች።
መንግሥት የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ ነው
Jul 9, 2026 735
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ መሆኑን አስተያየታቸውን የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግሥት የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ለመገንባት ሁልጊዜም ቢሆን የሰላም በር ክፍት ማድረጉን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይል ከምንጊዜውም በላይ በአስተማማኝ ቁመና ላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊትም በላቀ ቴክኖሎጂና በሰው ኃይል በጽኑ መሠረት መገንባቱን አብራርተዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል እንደሌለም ነው አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም፤ የኢትዮጵያን ሰላም፣ ልማትና ዕድገት ለማደናቀፍ የሚጥሩ የውስጥ ኃይሎች ፍላጎት ፈጽሞ አይሳካም ብለዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ትንኮሳ የሚፈጽም አንዳች ኃይል ቢኖር እንኳን ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ደኅንነት ለማስከበር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ገዛኸኝ ደበበ፤ ቅድመ አያቶች በከፈሉት ውድ መስዋዕትነት ትውልዱ ሉዓላዊ ነፃነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን እንዲረከብ ማስቻሉን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅትም ዜጎች በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ክብር ላይ ሊቃጣ የሚችልን አንዳች ትንኮሳ ለመቀልበስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመሸከም ኢትዮጵያን ለማወክ የሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ ኃይሎችም፣ ውይይትና ምክክርን በማስቀደም ለሀገር ሉዓላዊ ክብር በጋራ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ፀሐይ አሰፋ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአጭር ዓመታት ውስጥ በሁሉም ዘርፍ አስደማሚ የልማት ውጤት እያስመዘገበች እንደሚገኝ ገልጸዋል። በጫካ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበል፣ ውይይትና ምክክርን አስቀድመው ለኢትዮጵያ ዕድገት መፋጠን በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። በሁሉም ዘርፍ የሚመዘገበው የኢትዮጵያ የልማት ውጤት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በጸሎት ዮሐንስ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ልማት በማስቀጠል፣ ለሀገር ሉዓላዊ ደኅንነት ከመንግሥት ጋር በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል። ቅድመ አያቶች በዓድዋ፤ የአሁኑ ትውልድ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬት ያደረጉት በሕብር የታተመ አንድነትም፣ ማንኛውንም የውጭ ትንኮሳና ጫና መቀልበስ እንደሚቻል ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ሌላኛዋ የመዲናዋ ነዋሪ ፀሐይ ተፈራ በበኩላቸው፤ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሚሰጠው ተደጋጋሚ ዕድል የሀገር ልማትና ዕድገትን ለማስቀጠል የሚመነጭ ቁርጠኛ አቋም መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም የሀገርን ሰላምና ዕድገት ለማስቀጠል ከመንግሥት ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ በትብብር መስራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት።
ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ቀጣናዊ ግቦች እንዲሳኩ ከአባል ሀገራት ጋር በትብብር መስራቷን ታጠናክራለች
Jul 9, 2026 709
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ቀጣናዊ ግቦች እንዲሳኩ ከአባል ሀገራት ጋር በትብብር መስራቷን እንደምታጠናክር የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር 22ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያውን ወደ ሥራ ለማስገባትና የትስስሩን ተቋማዊ እድገት ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ጠቅሰዋል። ትስስሩን ለመምራት ኢትዮጵያ በሊቀ-መንበርነት መመረጧን አስታውሰው፤ የተጀመሩ ቀጣናዊ ጥረቶችን ለማስቀጠል ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ የትስስሩን በተቋማዊ ታማኝነት፣ በቀጣናዊ አንድነትና በሕግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ የተቀናጀ ገበያ የመፍጠር የጋራ ግብን ለማሳካት ከሁሉም አባል ሀገራት ጋር ትብብሯን እንደምታጠናክር አመልክተዋል። የጋራ ቁርጠኝነትን በማጉላት፣ ለአባል ሀገሮች ሁሉ ጥቅም ሲባል ድርጅታችንንም ሆነ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያችንን ለማጠናከር የተገኘውን መልካም አጋጣሚ ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ደኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ሱዳን ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ሚናዋን እየተወጣች ነው ብለዋል። በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ማዕቀፍም ቀጣናውን በኃይል የማስተሳሰር ሚናዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ በአባል ሀገራቱ መካከል በጋራ ለመስራት የተደረሱ ስምምነቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ውሎችን ጨምሮ በተለያዩ አሰራሮች ላይ ውይይት ተደርጎ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል። በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ገበያ ማዕከሉ ቦታ ለመወሰን ሌላው የጉባኤው ዋና የውይይት አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር 13 ሀገራትን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን፤ በአባል ሀገራቱ መካከል የኤሌክትሪክ ኃይልን በጋራ ለመጠቀም፣ የኃይል ግብይት ለማካሄድ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ታልሞ የተመሠረተ ነው። ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛንያ፣ ኡጋንዳ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊያና ሊቢያ የትስስሩ አባል ሀገራት ናቸው።
ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው
Jul 9, 2026 649
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የተከማቹ ችግሮችን የሚፈታ በመሆኑ ዕድሉን መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በምክክሩ ሂደት ከታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል ጀምሮ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ አጀንዳ የተለየበት መሆኑን ጠቁመው፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን ጠቃሚ ሒደት ነው ብለዋል። የምክክሩ ዋና ዓላማ ባለፉት ዘመናት ለቅራኔ ምንጭ የሆኑና የተከማቹ ችግሮችን በጋራ መክሮ መልክ ማስያዝ እንደሆነ ጠቅሰው፣ አዲስ ማኅበራዊ ውል የሚፈጸምበት መሆኑንም አመልክተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያና የሀገራዊ ምክክር ሂደትን አስመልክቶ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች፤ ምክክር የችግሮችን መንስኤና መፍትሔ በትክክል ለመለየት የሚያስችል ቀዳሚ መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩንና ታሪካዊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መካሄድ፣ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስታውቀዋል። ይህ ወሳኝ ምዕራፍ ስኬታማ እንዲሆንም ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በንቃትና በኃላፊነት ስሜት ሊሳተፍ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ሰላማዊት ጌትነት እንደተናገሩት፤ ምክክር በሀገር ውስጥ ያሉ ችግሮችንና መፍትሔዎቻቸውን በግልጽ ለመለየት ያስችላል። በኢትዮጵያ የሚካሄደው ምክክር ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የተረጋጋች ሀገርን ለመገንባት ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑን አንስተዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ያሬድ ደምሌ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አለመግባባቶችን በመፍታት የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠናከረ ሀገር መገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ ጦርነትና ግጭት ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጡ መታወቅ እንዳለበት የገለጹት አቶ ያሬድ፤ ምክክሩ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥና የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ወሳኝ ሚና እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል። አቶ ኃይሌ ባህረ፤ ሃገራዊ ምክክሩ የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ መሣሪያ መሆኑን በመጥቀስ በሀገሪቱ ያሉ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግሮ ለመፍታት የሚያስችል ምቹ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ወይዘሮ ወሰንየለሽ ገብሩ በበኩላቸው፤ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የምክክር ባህልን ማሳደግ አማራጭ የሌለው ተግባር በመሆኑ የሚደረገው ምክክር ለዘላቂ ሰላም ሆነ ልማትን ለማስቀጠል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ስታከናውነው የቆየችው የሀገራዊ ምክክር ሂደት አሁን ላይ የመጨረሻና ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተመካካሪዎች አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሚያከናውኗቸው ተግባራት የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ሊያጎለብቱ ይገባል
Jul 9, 2026 682
ሰመራ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሚያከናውኗቸው ተግባራት የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አመለከተ። በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በአፈፃፀም ሪፖርትና በቅንጅታዊ ተግባራት ዕቅድ ላይ በሰመራ ከተማ ውይይት አድርገዋል። በወቅቱም የአፋር ክልል ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደረሳ መሐመድ እንደገለፁት፤ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚያከናውኗቸው ተግባራት የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ሊያጎለብቱ ይገባል። ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ ድርጅቶቹ እርስ በርስ ተናበውና ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ አመልክተዋል። ባለፈው በጀት ዓመት በክልሉ ድርጅቶቹ 60 ዋና ዋና ፕሮጀክቶችን ያከናወኑ መሆኑን ገልጸው ለፕሮጀክቶቹም በአጠቃላይ 6 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉን አስረድተዋል። ከፕሮጀክቶቹ መካከል 18ቱ በጤናና በሥነ-ምግብ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን አብራርተዋል። ድርጅቶቹ በሚያከናውኗቸው የልማት ሥራዎች የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጨባጭ ፍላጎት ከማገናዘብ ባለፈ የሥራ ዕድሎችን ማመቻቸት እንደሚገባቸውም ምክትል ኃላፊው አመልክተዋል። በክልሉ በተከናወኑ የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች ዘርፎች ድርጅቶቹ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ጉልህ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንኑ ኅብረተሰብን ማዕከል ያደረገ ድጋፋቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም አሳስበዋል። የ"ፍሬንድሺፕ ሰፖርት አሶሴሽን" ፕሮግራም ማናጀር ወይዘሮ የማ ዳንኤል በበኩላቸው፤ ፕሮግራሙ በጤና፣ በውሃና በሰላም ግንባታ ዘርፎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማላቅ በትጋት እንደሚሰሩም ተናግረዋል። በክልሉ በተለያዩ ወረዳዎች በሕዝብና እንስሳት ጤና ዘርፎች እንዲሁም በውሃ ላይ በመሰማራት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ያጎለበቱ በርካታ ተግባራትን እንዳከናወኑ የገለጹት ደግሞ "ኮፕ" (COOP) በተሰኘው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት የአፋር ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ መሐመድ ጎንፍሬ ናቸው። በበጀት ዓመቱ ድርጅቶቹ በክልሉ በሚገኙ ስድስት ዞኖች ውስጥ በስፋት ተሰማርተው፣ ማኅበረሰብ ተኮር የሆኑ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በስኬት ማከናወናቸውም ተገልጿል።
ፖለቲካ
መንግሥት የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ ነው
Jul 9, 2026 735
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ መሆኑን አስተያየታቸውን የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግሥት የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ለመገንባት ሁልጊዜም ቢሆን የሰላም በር ክፍት ማድረጉን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይል ከምንጊዜውም በላይ በአስተማማኝ ቁመና ላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊትም በላቀ ቴክኖሎጂና በሰው ኃይል በጽኑ መሠረት መገንባቱን አብራርተዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል እንደሌለም ነው አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም፤ የኢትዮጵያን ሰላም፣ ልማትና ዕድገት ለማደናቀፍ የሚጥሩ የውስጥ ኃይሎች ፍላጎት ፈጽሞ አይሳካም ብለዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ትንኮሳ የሚፈጽም አንዳች ኃይል ቢኖር እንኳን ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ደኅንነት ለማስከበር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ገዛኸኝ ደበበ፤ ቅድመ አያቶች በከፈሉት ውድ መስዋዕትነት ትውልዱ ሉዓላዊ ነፃነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን እንዲረከብ ማስቻሉን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅትም ዜጎች በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ክብር ላይ ሊቃጣ የሚችልን አንዳች ትንኮሳ ለመቀልበስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመሸከም ኢትዮጵያን ለማወክ የሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ ኃይሎችም፣ ውይይትና ምክክርን በማስቀደም ለሀገር ሉዓላዊ ክብር በጋራ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ፀሐይ አሰፋ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአጭር ዓመታት ውስጥ በሁሉም ዘርፍ አስደማሚ የልማት ውጤት እያስመዘገበች እንደሚገኝ ገልጸዋል። በጫካ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበል፣ ውይይትና ምክክርን አስቀድመው ለኢትዮጵያ ዕድገት መፋጠን በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። በሁሉም ዘርፍ የሚመዘገበው የኢትዮጵያ የልማት ውጤት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በጸሎት ዮሐንስ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ልማት በማስቀጠል፣ ለሀገር ሉዓላዊ ደኅንነት ከመንግሥት ጋር በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል። ቅድመ አያቶች በዓድዋ፤ የአሁኑ ትውልድ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬት ያደረጉት በሕብር የታተመ አንድነትም፣ ማንኛውንም የውጭ ትንኮሳና ጫና መቀልበስ እንደሚቻል ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ሌላኛዋ የመዲናዋ ነዋሪ ፀሐይ ተፈራ በበኩላቸው፤ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሚሰጠው ተደጋጋሚ ዕድል የሀገር ልማትና ዕድገትን ለማስቀጠል የሚመነጭ ቁርጠኛ አቋም መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም የሀገርን ሰላምና ዕድገት ለማስቀጠል ከመንግሥት ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ በትብብር መስራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት።
ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው
Jul 9, 2026 649
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የተከማቹ ችግሮችን የሚፈታ በመሆኑ ዕድሉን መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በምክክሩ ሂደት ከታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል ጀምሮ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ አጀንዳ የተለየበት መሆኑን ጠቁመው፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን ጠቃሚ ሒደት ነው ብለዋል። የምክክሩ ዋና ዓላማ ባለፉት ዘመናት ለቅራኔ ምንጭ የሆኑና የተከማቹ ችግሮችን በጋራ መክሮ መልክ ማስያዝ እንደሆነ ጠቅሰው፣ አዲስ ማኅበራዊ ውል የሚፈጸምበት መሆኑንም አመልክተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያና የሀገራዊ ምክክር ሂደትን አስመልክቶ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች፤ ምክክር የችግሮችን መንስኤና መፍትሔ በትክክል ለመለየት የሚያስችል ቀዳሚ መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩንና ታሪካዊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መካሄድ፣ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስታውቀዋል። ይህ ወሳኝ ምዕራፍ ስኬታማ እንዲሆንም ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በንቃትና በኃላፊነት ስሜት ሊሳተፍ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ሰላማዊት ጌትነት እንደተናገሩት፤ ምክክር በሀገር ውስጥ ያሉ ችግሮችንና መፍትሔዎቻቸውን በግልጽ ለመለየት ያስችላል። በኢትዮጵያ የሚካሄደው ምክክር ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የተረጋጋች ሀገርን ለመገንባት ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑን አንስተዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ያሬድ ደምሌ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አለመግባባቶችን በመፍታት የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠናከረ ሀገር መገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ ጦርነትና ግጭት ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጡ መታወቅ እንዳለበት የገለጹት አቶ ያሬድ፤ ምክክሩ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥና የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ወሳኝ ሚና እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል። አቶ ኃይሌ ባህረ፤ ሃገራዊ ምክክሩ የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ መሣሪያ መሆኑን በመጥቀስ በሀገሪቱ ያሉ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግሮ ለመፍታት የሚያስችል ምቹ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ወይዘሮ ወሰንየለሽ ገብሩ በበኩላቸው፤ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የምክክር ባህልን ማሳደግ አማራጭ የሌለው ተግባር በመሆኑ የሚደረገው ምክክር ለዘላቂ ሰላም ሆነ ልማትን ለማስቀጠል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ስታከናውነው የቆየችው የሀገራዊ ምክክር ሂደት አሁን ላይ የመጨረሻና ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተመካካሪዎች አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡
መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር መስፋት የሰጠው ትኩረት ለሀገር ዕድገት በትብብር መሥራትን የሚያጠናክር ነው
Jul 9, 2026 589
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር መስፋት የሰጠው ትኩረት ለሀገር ዕድገት በትብብር መሥራትን የሚያጠናክር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በገዥው ፓርቲ ብልፅግና እና በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ የመሥራትና ሚዛኑን የጠበቀ የፉክክርና የትብብር ምህዳር ተገንብቷል። በዚህም የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ተመድበው እየሠሩ ሲሆን ይህም አካታች የፖለቲካ ጉዞን ከመክፈቱ በላይ ሀገርን በጋራ የማገልገል የትብብር አቅምን አሳድጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በሰጡት ማብራሪያ፥ ብልፅግና ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ 85 በመቶ በሆኑ ወንበሮች ላይ ብቻ በመወዳደር፣ በቀሪው 15 በመቶ ወንበር ላይ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻቸውን እንዲወዳደሩ ዕድል መስጠቱን ተናግረዋል። በምርጫው በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሳተፋቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር ግንባታ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፥ መንግሥት ለአሳታፊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚያደርገው ጥረት፤ ለሀገራዊ መግባባት፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመሥራትና ለአካታች ፖለቲካ ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም ጠቁመዋል። ወይዘሮ መታሰቢያ ጠብቀው፤ 15 በመቶ ወንበሮች ላይ ሳይወዳደር ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻ ክፍት ማድረጉ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ይሁነኝ ብሎ እየሠራ መሆኑን ያስመሰከረ ነው ብለዋል። ሁሉንም ያሳተፈ ሥርዓት መገንባት፣ መንግሥት የጀመራቸውን የልማት ሥራዎች በትብብር ለማፋጠንና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ ለመሥራት አቅም መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ሴቶች ወደ አመራርነት የመምጣት አጋጣሚያቸው እጅግ ውስን የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በሁሉም ዘርፎች እኩል ተሳታፊ መሆን መቻላቸው ሌላው የአካታችነት መገለጫ መሆኑን ጠቁመዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ዳዊት ይርባ በበኩላቸው፤ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማጠናከር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል። የመንግሥት ቁርጠኝነት በሐሳብ ልዕልና ላይ የተመሠረተ ፉክክርና ትብብርን በማስፋት ለዘላቂ ሰላምና ልማት መሠረት እንደሚሆን ጠቁመዋል። ወይዘሮ ውበት ደጉ በበኩላቸው፤ አሳታፊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዜጎች ሐሳባቸውን በነፃነት በመግለጽ ለሀገራቸው ልማትና ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ዕድል እንደሚፈጥር አብራርተዋል። አቶ ሺመልስ ከተማም መንግሥት በተባበረ መንፈስ ለመሥራትና ለአካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያሳየው ቁርጠኝነት በሀገሪቱ የፖለቲካ ጉዞ ትልቅ ተስፋን የሚዘራ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በእያንዳንዱ ዜጋ ዘንድ መደማመጥ፣ መግባባትና መተሳሰብን እንደሚፈጥር እምነታቸውን ገልጸዋል። አሳታፊ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታው ዘላቂ እንዲሆን የውይይት ባህል ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ ዶክተር ፍቅሩ ደስታ ናቸው። መንግሥት ሁሉንም ያሳተፈ እና በውይይት ላይ የተመሠረተ አካሄድ ለመከተል ቁርጠኛ መሆኑ ዘላቂ ሰላምና መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው አስገንዝበዋል።
ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልል ተተኪ ትውልድን ሆን ብሎ በመዋቅራዊ አሰራር እያጠፋና እያመከነ ነው
Jul 9, 2026 730
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልል ተተኪ ትውልድን ሆን ብሎ በመዋቅራዊ አሰራር እያጠፋና እያመከነ መሆኑን የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባል ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ገለጹ። ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን "ፅምዶ" በሚል ስያሜ ከሻዕቢያ፣ ከሱዳንና ከሀገር ውስጥ ፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያን እያተራመሰ ለመኖር አልሞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም አስታውቀዋል። ቡድኑ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት እያጣቀሰ ለዳግም ጦርነት ጊዜ መግዣነት በመጠቀም የትግራይ እናቶችን እያስለቀሰ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም የትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታን አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የጥይት ድምፅ በማጥፋት ለክልሉ ሕዝብ ተስፋ የሰጠ ሁነኛ የሰላም በር ነበር። የፌዴራል መንግሥትም በሰላም ስምምነቱ መሠረት የወደሙ መሠረተ ልማቶችንና ተቋማትን መልሶ መገንባቱን ገልጸው፤ ይህም የክልሉ ሕዝብ የተረጋጋና ሰላማዊ ሕይወት የሚመራበትን ዕድል እንደፈጠረ አብራርተዋል። ይህም የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር በማቋቋም ጭምር ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ተቋማት በአፋጣኝ ወደ አገልግሎት እንዲመለሱ ማድረጉን አስታውሰዋል። የቀድሞ የትግራይ ክልል ታጣቂዎችንም በተሃድሶ ስልጠና በማሳለፍ፣ ወደ ማኅበረሰባቸው ተቀላቅለው የተረጋጋ ሕይወት የሚመሩበት የገንዘብ ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱንም አክለዋል። ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን ለትግራይ ሕዝብ ትልቅ እፎይታን ይዞ የመጣውን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ለጊዜ መግዣነት እንደተጠቀመበት ተናግረዋል። በዚህም ቡድኑ የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር በኃይልና በተደጋጋሚ በማፍረስ፣ በጨረባ ምርጫ ያደራጀውን ሕገ-ወጥ ምክር ቤት በመሰብሰብ ተቀባይነቱን ያጣ ካቢኔ ማዋቀሩን አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅትም ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልል ተተኪ ትውልድን ሆን ብሎ በመዋቅራዊ አሰራር እያጠፋ መሆኑን ወይዘሮ ኬሪያ አስረድተዋል። በተለይም ራሱን ለዳግም ጦርነት በማዘጋጀት፣ ሕፃናትን ከእናታቸው ጉያ በመንጠቅ የትግራይ እናቶችን የደም እምባ እያስለቀሰ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ቡድኑ ከሀገር ውስጥና ከውጭ የጠላት ኃይሎች ጋር ያልተቀደሰ ጋብቻ በመፍጠር፣ የትግራይ ክልል ሕዝብን ለዳግም ጉስቁልና ለማመቻቸት ጥረት እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። ይህ ህገ ወጥ ቡድን በትግራይ ሕዝብ ላይ እያደረሰ የሚገኘው ከፍተኛ ሰብዓዊ በደልም በተለያዩ ሀገራትና በዓለም አቀፍ ተቋማት ጭምር እየተወገዘ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ቡድኑ "ፅምዶ" በሚል ስያሜ ከሻዕቢያ፣ ከሱዳንና ከሀገር ውስጥ ፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያን እያተራመሰ ለመኖር አልሞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አንስተዋል። የትግራይ ክልል እናቶች በፅንፈኛው የሕወሓት ቡድን ላይ ድንጋይ እየወረወሩ ነው ያሉት ወይዘሮ ኬሪያ፤ የክልሉ ወጣትና ሕዝብም የቡድኑን እኩይ ሴራ በስፋት እየታገለ መሆኑን አስረድተዋል። ከሻዕቢያ ጋር ከሚፈጽመው የወርቅና የከበሩ ማዕድናት ምዝበራ ባሻገር፣ የትግራይ ወጣቶችን ለሱዳን ጦርነት በመሸጥ የውጭ ምንዛሬ ገቢን የጦር መሣሪያ መግዣ እያደረገ መሆኑን አጋልጠዋል። በተጨማሪም በፍጹም ጭካኔ ሕፃናትን ከእናት ጉያ በመንጠቅና ወደ ጦር ካምፕ በማጋዝ፣ በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ የሕግ ድንጋጌ የሚያስጠይቅ ሰብዓዊ ግፍ እየፈጸመ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ተቋማትና ዜጎች የሚደርስበትን ውግዘት ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት፣ የክልሉን ሕዝብ ወደ ባሰ ጥፋት እየመራው ይገኛል ብለዋል። የሀገር ሽማግሌዎች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማትና ሀገራት የቡድኑን እኩይ ሴራ ሊታገሉት እንደሚገባ ተናግረዋል። የክልሉን ትምህርት ቤቶችም አስቀድሞ በመዝጋትና ወጣቱን ወደ ጦር ካምፕ በማጋዝ የትግራይን ተተኪ ትውልድ እያመከነ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናንም "እራሴ አዘጋጃለሁ" በሚል፣ የወጣቱን የነገ ተስፋና ሕልም እያጨለመ መሆኑን አንስተዋል። ይህም ቡድኑ ሆን ብሎ የትግራይ ክልልን ተተኪ ትውልድ በመዋቅር እያጠፋ እንደሚገኝ ማሳያ ነው ብለዋል።
የመንግስት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ግጭትን በዘላቂነት ለማስቆምና ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ቁርጠኝነቱን የሚያሳይ ነው
Jul 9, 2026 650
ገንዳውኃ፣ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፡- የመንግስት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ግጭትን በዘላቂነት ለማስቆምና ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ቁርጠኝነቱን የሚያሳይ መሆኑን በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳውሃ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር በሰጡት ማብራሪያ መንግስት ችግሮችን በውይይት ለመፍታት የተያዘውን ጠንካራ አቋም መግለፃቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ለዘላቂ ሰላም፣ ለንግግርና ውይይት መንግስት ሁል ጊዜም ዝግጁ መሆኑን አንስተው የግጭትና ጦርነት እሳቤ አውዳሚና ትርፍ የሌለው ስለመሆኑ ተናግረዋል። በመሆኑም የመንግስት የሰላም በር ሁልጊዜም ክፍት መሆኑን ገልጸው ሰላምን ለሚመርጡ ሁሉ ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጠዋል። በአማራ ክልል ምእራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውሃ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች የመንግስት የሰላም ጥረትና ቁርጠኝነት የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩም ማብራሪያ መንግስት ለሰላም ያለውን ጠንካራ አቋምና በጥፋት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ውለው ሳያድሩ እንዲመለሱ እድል የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወይዘሮ ትግስት እማኘው፣ ወጣት ገብረኪዳን መንጋው እና አቶ ኪሩቤል መንግስቴ፤ የመንግስት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ግጭትን በዘላቂነት ለማስቆምና ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ቁርጠኝነቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። በተለይም በአማራ ክልል ህዝቡ ዘላቂ ሰላምና ልማት ይፈልጋል ያሉት ነዋሪዎቹ መንግስት ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት የተረጋጋች ሀገር ለመገንባት የሚያደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። የመንግስት የሰላም ጥረት የሀገርና የህዝብ አንድነት ለማጠናከር፣ ሰላምን ለማስፈንና ልማትን ለማፋጠን መሰረት የሚያኖር መሆኑን ነው የተናገሩት። የመንግስትን የሰላም ጥረት በማገዝና በመደገፍ አካባቢያውን ከጸረ ሰላም ቡድኖች ለመጠበቅ የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ያለው የሰብዓዊ መብት ረገጣ ተባብሶ ቀጥሏል-ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት
Jul 9, 2026 753
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- ህገ-ወጡ የህወሃት ቡድን የሰላም ስምምነቱን በማፍረስ በትግራይ ክልል የሰብዓዊ መብት ረገጣውን እያባባሰ መምጣቱን የመጀመሪያው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ የነበሩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ገለጹ፡፡ የመጀመሪያው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ የነበሩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ወቅታዊውን የትግራይ ክልል ሁኔታ አስመልክቶ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች ሁለንተናዊ እድላቸው እየጠበበና በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እየገቡ ነው። ቡድኑ ወጣቶችን በተለያየ መልክ ለጦርነት መማገጃነትና ለውክልና ጦርነት እየተጠቀመባቸው እንደሚገኝም አጋልጠዋል። የሰብዓዊ መብት ረገጣው ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ እጅግ እየከፋና ጫፍ ላይ መድረሱንም ገልፀው፤ በርካታ ወጣቶች በግድ እየታፈሱ ወደ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየተወሰዱ መሆኑን አስረድተዋል። ከዚህም አልፎ ወደ አዲስ አበባ ለመውጣት የሚሞክሩ ተጓዦችን ጭምር በየመንገዱ ከነበሩበት ተሽከርካሪ እያስወረዱ ወደ ስልጠና የሚወስዱበት፣የሚያስሩበትና እስከ ሞት ቅጣት የሚደርስ እርምጃ የሚፈጽሙበት ሁኔታ መኖሩን ጠቅሰዋል። የቡድኑን ፍላጎት የማይቀበሉ በርካታ ወላጆችም በየአካባቢው ለእስር እየተዳረጉ ይገኛሉ ሲሉ ተናግረዋል። ታጣቂዎች ወጣቶች ትምህርታቸውን በግድ እንዲያቋርጡ በማድረግ በካምፕ ውስጥ በማሰልጠን ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በዚህም ምክንያት በትግራይ ክልል ውስጥ መደበኛ የልማትና የዴሞክራሲ እንቅስቃሴ ጠፍቶ ህዝቡ ወደ ውጭ ሀገራት እንዲሰደድ እየተገደደ ነው ብለዋል። ይህ ህዝብን አሸብሮና አስገድዶ ወታደር የማድረግ ዓላማ ከሻዕቢያ የተኮረጀና የተማሩት ትምህርት ነው ያሉት ፕሮፌሰር ክንደያ፤በአሁኑ ወቅት ድርጊቱ በፍጥነትና በስፋት እየተገበረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በትግራይ ህዝብ ዘንድ ስለ ሰላምና ዴሞክራሲ ሳይሆን ስለ ራሱ ህልውና ብቻ የሚጠይቅበት አስገዳጅ ሁኔታ መፈጠሩን ጠቁመዋል። ይህ በትግራይ ክልል ውስጥ ችግር እየፈጠረ ያለው ቡድን በአስቸኳይ ተጠያቂ የሚሆንበት አሰራር ሊዘረጋ እንደሚገባ ፕሮፌሰሩ አሳስበዋል። መገናኛ ብዙሃን ሰላም እንዲመጣ በትግራይ ክልል ያለውን እውነተኛ ጥፋት ለህዝብ በማጋለጥ በቁርጠኝነት መስራትና መታገል ይኖርባቸዋል ሲሉ አስገንዝበዋል።
መንግሥት ለታጠቁ ኃይሎች የሚያቀርበው ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ለሀገር ዘላቂ ሰላም ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው
Jul 9, 2026 675
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦መንግሥት ለታጠቁ ኃይሎች የሚያቀርበው ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ለሀገር ዘላቂ ሰላም ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ መሆኑን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግስት ለዘላቂ ሰላም፣ ለንግግርና ውይይት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን አስረድተዋል። የግጭትና የጦርነት እሳቤ አውዳሚና ትርፍ የሌለው መሆኑን በአሁኑ ወቅት ለሀገር የሚያስፈልገው ሰላም፣ ትብብርና አብሮነት መሆኑን በማብራሪያቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። መንግሥት ዛሬም ቢሆን በጫካ ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች ጋር ለመወያየትና ለሰላም ያለው በር ክፍት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰጡት ማብራሪያ ተከትሎ ኢዜአ ያነጋገርናቸው የመዲናዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ መንግስት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ የሚያደርገው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡ ከነዋሪዎች መካከል ተስፋዬ ጸጋዬ እንዳሉት፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰላም ዙሪያ የሰጡት ማብራሪያ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ያለውን ጽኑ አቋም ያሳየበት ነው። መንግሥት በጫካ ለሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎች በተደጋጋሚ የሚያቀርበውን የሰላም ጥሪ ለአብነት አንስተዋል። በመሆኑም የታጠቁ ኃይሎች ይህንን የመንግሥት ጥሪ በአዎንታ በመቀበል ለዘላቂ ሰላምና ልማት የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተመሳሳይ አቶ ፍቃዱ ንጉሤ፤ የግጭትና የጦርነት እሳቤ አውዳሚና ትርፍ የሌለው መሆኑን በመገንዘብ፣ የታጠቁ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ መቀበል እንዳለባቸው አስታውቀዋል። በልማት የተገኘውን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ ዘላቂ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ለሁለንተናዊ ዕድገትና ለጋራ ተጠቃሚነት መሥራት እንደሚገባ የገለጹት ደግሞ አቶ አስናቀ ለጪሳ ናቸው። የታጠቁ ኃይሎች መንግሥት ለሰላም የከፈተውን በር በአግባቡ በመጠቀም ለአገር ልማትና ብልጽግና በትጋት መሥራት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
በጠመንጃ አፈሙዝ ስልጣን ለመያዝ መሞከር ጊዜው ያለፈበት ኋላ ቀር እሳቤ ነው-የአብን ምክትል ሊቀመንበር
Jul 9, 2026 810
ባህር ዳር፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በጠመንጃ አፈሙዝ ስልጣን ለመያዝ መሞከር ጊዜው ያለፈበት ኋላ ቀር እሳቤ መሆኑን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ምክትል ሊቀመንበር መልካሙ ፀጋዬ ገለጹ። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ስርአት ተለውጦ አካታችና አሳታፊ በመሆኑ በሀገሩ ጉዳይ ላይ ሁሉም በእኩልነት የሚሳተፍበት ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ተፈጥሯል። በኢትዮጵያ አጋር ተብለው የዳር ተመልካች የነበሩ ክልሎች አሁን ላይ እኩል ተሳታፊ ሆነው በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እየወሰኑ ነው። በውጭና በሀር ውስጥ መሰረታቸውን አድርገው በትጥቅ ትግል ውስጥ የነበሩ ወገኖችም የለውጡ መንግስት የፈጠረውን ምቹ መደላድል ተጠቅመው በሰላማዊ ትግል ቀጥለዋል። የፖለቲካ ስርአቱ በዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት እየዳበረ በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባት ስራም በመከናወን ላይ ይገኛል። እነዚህን መልካም እድሎች በመግፋት በጠመንጃ ለጥያቄያችን መልስ እናገኛለን፤ አሸንፈንም ስልጣን እንይዛለን በማለት በጫካ የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኞች ይስተዋላሉ። በመሆኑም በዚህ ዘመን በኢትዮጵያ ከሰላማዊ የትግል ስልት ውጭ የትኛውም አይነት የሀይል እንቅስቃሴ አክሳሪና የማያዋጣ መሆኑን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ምክትል ሊቀመንበር መልካሙ ፀጋዬ ገልጸዋል። በዚህ ዘመን በምክክር ችግሮችን የመፍታት እና በምርጫ ተወዳድሮ የማሸነፍ ሰፊ እድል እያለ በጫካ የሚደረግ የጠመንጃ እንቅስቃሴ በፍፁም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ፓርቲያችን በፅኑ ያምናል ብለዋል። በኢትዮጵያ በጠመንጃ ስልጣን ለመያዝ መሞከር ጊዜው ያለፈበት ኋላ ቀር እሳቤ በመሆኑንም ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የሃይል አማራጮችን በመተው በመቀራረብ በምክክር የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሁላችንም ዝግጁነትና ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ብለዋል። በተቃርኖ የከረሩ ዋልታ ረገጥ እሳቤዎችን በማለዘብ በምክክር ወደ መሀል በማምጣት ለችግሮቻችን ዘላቂ መፍትሄ ልናበጅ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘውን ሀገራዊ የምክክር እድል መጠቀም የትውልድንና የሀገርን ቀጣይ እጣ ፋንታ መወሰን ይገባናል ብለዋል። በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የተለዩ አጀንዳዎች የዜጎችን የዘመናት ጥያቄዎች ጭምር ማእከል ያደረጉ በመሆኑ ለስኬታማነቱ መስራት የሁላችንም ሃላፊነት ነው ሲሉ አቶ መልካሙ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ሃሳብ ለማካተት ጥረት የተደረገበት መሆኑን አንስተው እድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ማለታቸው ይታወሳል።
ፖለቲካ
መንግሥት የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ ነው
Jul 9, 2026 735
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ መሆኑን አስተያየታቸውን የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግሥት የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ለመገንባት ሁልጊዜም ቢሆን የሰላም በር ክፍት ማድረጉን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይል ከምንጊዜውም በላይ በአስተማማኝ ቁመና ላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊትም በላቀ ቴክኖሎጂና በሰው ኃይል በጽኑ መሠረት መገንባቱን አብራርተዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል እንደሌለም ነው አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም፤ የኢትዮጵያን ሰላም፣ ልማትና ዕድገት ለማደናቀፍ የሚጥሩ የውስጥ ኃይሎች ፍላጎት ፈጽሞ አይሳካም ብለዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ትንኮሳ የሚፈጽም አንዳች ኃይል ቢኖር እንኳን ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ደኅንነት ለማስከበር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ገዛኸኝ ደበበ፤ ቅድመ አያቶች በከፈሉት ውድ መስዋዕትነት ትውልዱ ሉዓላዊ ነፃነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን እንዲረከብ ማስቻሉን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅትም ዜጎች በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ክብር ላይ ሊቃጣ የሚችልን አንዳች ትንኮሳ ለመቀልበስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመሸከም ኢትዮጵያን ለማወክ የሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ ኃይሎችም፣ ውይይትና ምክክርን በማስቀደም ለሀገር ሉዓላዊ ክብር በጋራ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ፀሐይ አሰፋ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአጭር ዓመታት ውስጥ በሁሉም ዘርፍ አስደማሚ የልማት ውጤት እያስመዘገበች እንደሚገኝ ገልጸዋል። በጫካ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበል፣ ውይይትና ምክክርን አስቀድመው ለኢትዮጵያ ዕድገት መፋጠን በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። በሁሉም ዘርፍ የሚመዘገበው የኢትዮጵያ የልማት ውጤት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በጸሎት ዮሐንስ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ልማት በማስቀጠል፣ ለሀገር ሉዓላዊ ደኅንነት ከመንግሥት ጋር በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል። ቅድመ አያቶች በዓድዋ፤ የአሁኑ ትውልድ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬት ያደረጉት በሕብር የታተመ አንድነትም፣ ማንኛውንም የውጭ ትንኮሳና ጫና መቀልበስ እንደሚቻል ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ሌላኛዋ የመዲናዋ ነዋሪ ፀሐይ ተፈራ በበኩላቸው፤ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሚሰጠው ተደጋጋሚ ዕድል የሀገር ልማትና ዕድገትን ለማስቀጠል የሚመነጭ ቁርጠኛ አቋም መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም የሀገርን ሰላምና ዕድገት ለማስቀጠል ከመንግሥት ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ በትብብር መስራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት።
ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው
Jul 9, 2026 649
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የተከማቹ ችግሮችን የሚፈታ በመሆኑ ዕድሉን መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በምክክሩ ሂደት ከታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል ጀምሮ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ አጀንዳ የተለየበት መሆኑን ጠቁመው፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን ጠቃሚ ሒደት ነው ብለዋል። የምክክሩ ዋና ዓላማ ባለፉት ዘመናት ለቅራኔ ምንጭ የሆኑና የተከማቹ ችግሮችን በጋራ መክሮ መልክ ማስያዝ እንደሆነ ጠቅሰው፣ አዲስ ማኅበራዊ ውል የሚፈጸምበት መሆኑንም አመልክተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያና የሀገራዊ ምክክር ሂደትን አስመልክቶ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች፤ ምክክር የችግሮችን መንስኤና መፍትሔ በትክክል ለመለየት የሚያስችል ቀዳሚ መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩንና ታሪካዊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መካሄድ፣ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስታውቀዋል። ይህ ወሳኝ ምዕራፍ ስኬታማ እንዲሆንም ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በንቃትና በኃላፊነት ስሜት ሊሳተፍ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ሰላማዊት ጌትነት እንደተናገሩት፤ ምክክር በሀገር ውስጥ ያሉ ችግሮችንና መፍትሔዎቻቸውን በግልጽ ለመለየት ያስችላል። በኢትዮጵያ የሚካሄደው ምክክር ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የተረጋጋች ሀገርን ለመገንባት ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑን አንስተዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ያሬድ ደምሌ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አለመግባባቶችን በመፍታት የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠናከረ ሀገር መገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ ጦርነትና ግጭት ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጡ መታወቅ እንዳለበት የገለጹት አቶ ያሬድ፤ ምክክሩ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥና የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ወሳኝ ሚና እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል። አቶ ኃይሌ ባህረ፤ ሃገራዊ ምክክሩ የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ መሣሪያ መሆኑን በመጥቀስ በሀገሪቱ ያሉ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግሮ ለመፍታት የሚያስችል ምቹ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ወይዘሮ ወሰንየለሽ ገብሩ በበኩላቸው፤ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የምክክር ባህልን ማሳደግ አማራጭ የሌለው ተግባር በመሆኑ የሚደረገው ምክክር ለዘላቂ ሰላም ሆነ ልማትን ለማስቀጠል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ስታከናውነው የቆየችው የሀገራዊ ምክክር ሂደት አሁን ላይ የመጨረሻና ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተመካካሪዎች አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡
መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር መስፋት የሰጠው ትኩረት ለሀገር ዕድገት በትብብር መሥራትን የሚያጠናክር ነው
Jul 9, 2026 589
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር መስፋት የሰጠው ትኩረት ለሀገር ዕድገት በትብብር መሥራትን የሚያጠናክር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በገዥው ፓርቲ ብልፅግና እና በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ የመሥራትና ሚዛኑን የጠበቀ የፉክክርና የትብብር ምህዳር ተገንብቷል። በዚህም የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ተመድበው እየሠሩ ሲሆን ይህም አካታች የፖለቲካ ጉዞን ከመክፈቱ በላይ ሀገርን በጋራ የማገልገል የትብብር አቅምን አሳድጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በሰጡት ማብራሪያ፥ ብልፅግና ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ 85 በመቶ በሆኑ ወንበሮች ላይ ብቻ በመወዳደር፣ በቀሪው 15 በመቶ ወንበር ላይ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻቸውን እንዲወዳደሩ ዕድል መስጠቱን ተናግረዋል። በምርጫው በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሳተፋቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር ግንባታ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፥ መንግሥት ለአሳታፊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚያደርገው ጥረት፤ ለሀገራዊ መግባባት፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመሥራትና ለአካታች ፖለቲካ ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም ጠቁመዋል። ወይዘሮ መታሰቢያ ጠብቀው፤ 15 በመቶ ወንበሮች ላይ ሳይወዳደር ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻ ክፍት ማድረጉ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ይሁነኝ ብሎ እየሠራ መሆኑን ያስመሰከረ ነው ብለዋል። ሁሉንም ያሳተፈ ሥርዓት መገንባት፣ መንግሥት የጀመራቸውን የልማት ሥራዎች በትብብር ለማፋጠንና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ ለመሥራት አቅም መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ሴቶች ወደ አመራርነት የመምጣት አጋጣሚያቸው እጅግ ውስን የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በሁሉም ዘርፎች እኩል ተሳታፊ መሆን መቻላቸው ሌላው የአካታችነት መገለጫ መሆኑን ጠቁመዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ዳዊት ይርባ በበኩላቸው፤ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማጠናከር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል። የመንግሥት ቁርጠኝነት በሐሳብ ልዕልና ላይ የተመሠረተ ፉክክርና ትብብርን በማስፋት ለዘላቂ ሰላምና ልማት መሠረት እንደሚሆን ጠቁመዋል። ወይዘሮ ውበት ደጉ በበኩላቸው፤ አሳታፊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዜጎች ሐሳባቸውን በነፃነት በመግለጽ ለሀገራቸው ልማትና ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ዕድል እንደሚፈጥር አብራርተዋል። አቶ ሺመልስ ከተማም መንግሥት በተባበረ መንፈስ ለመሥራትና ለአካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያሳየው ቁርጠኝነት በሀገሪቱ የፖለቲካ ጉዞ ትልቅ ተስፋን የሚዘራ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በእያንዳንዱ ዜጋ ዘንድ መደማመጥ፣ መግባባትና መተሳሰብን እንደሚፈጥር እምነታቸውን ገልጸዋል። አሳታፊ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታው ዘላቂ እንዲሆን የውይይት ባህል ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ ዶክተር ፍቅሩ ደስታ ናቸው። መንግሥት ሁሉንም ያሳተፈ እና በውይይት ላይ የተመሠረተ አካሄድ ለመከተል ቁርጠኛ መሆኑ ዘላቂ ሰላምና መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው አስገንዝበዋል።
ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልል ተተኪ ትውልድን ሆን ብሎ በመዋቅራዊ አሰራር እያጠፋና እያመከነ ነው
Jul 9, 2026 730
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልል ተተኪ ትውልድን ሆን ብሎ በመዋቅራዊ አሰራር እያጠፋና እያመከነ መሆኑን የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባል ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ገለጹ። ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን "ፅምዶ" በሚል ስያሜ ከሻዕቢያ፣ ከሱዳንና ከሀገር ውስጥ ፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያን እያተራመሰ ለመኖር አልሞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም አስታውቀዋል። ቡድኑ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት እያጣቀሰ ለዳግም ጦርነት ጊዜ መግዣነት በመጠቀም የትግራይ እናቶችን እያስለቀሰ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም የትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታን አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የጥይት ድምፅ በማጥፋት ለክልሉ ሕዝብ ተስፋ የሰጠ ሁነኛ የሰላም በር ነበር። የፌዴራል መንግሥትም በሰላም ስምምነቱ መሠረት የወደሙ መሠረተ ልማቶችንና ተቋማትን መልሶ መገንባቱን ገልጸው፤ ይህም የክልሉ ሕዝብ የተረጋጋና ሰላማዊ ሕይወት የሚመራበትን ዕድል እንደፈጠረ አብራርተዋል። ይህም የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር በማቋቋም ጭምር ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ተቋማት በአፋጣኝ ወደ አገልግሎት እንዲመለሱ ማድረጉን አስታውሰዋል። የቀድሞ የትግራይ ክልል ታጣቂዎችንም በተሃድሶ ስልጠና በማሳለፍ፣ ወደ ማኅበረሰባቸው ተቀላቅለው የተረጋጋ ሕይወት የሚመሩበት የገንዘብ ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱንም አክለዋል። ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን ለትግራይ ሕዝብ ትልቅ እፎይታን ይዞ የመጣውን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ለጊዜ መግዣነት እንደተጠቀመበት ተናግረዋል። በዚህም ቡድኑ የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር በኃይልና በተደጋጋሚ በማፍረስ፣ በጨረባ ምርጫ ያደራጀውን ሕገ-ወጥ ምክር ቤት በመሰብሰብ ተቀባይነቱን ያጣ ካቢኔ ማዋቀሩን አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅትም ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልል ተተኪ ትውልድን ሆን ብሎ በመዋቅራዊ አሰራር እያጠፋ መሆኑን ወይዘሮ ኬሪያ አስረድተዋል። በተለይም ራሱን ለዳግም ጦርነት በማዘጋጀት፣ ሕፃናትን ከእናታቸው ጉያ በመንጠቅ የትግራይ እናቶችን የደም እምባ እያስለቀሰ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ቡድኑ ከሀገር ውስጥና ከውጭ የጠላት ኃይሎች ጋር ያልተቀደሰ ጋብቻ በመፍጠር፣ የትግራይ ክልል ሕዝብን ለዳግም ጉስቁልና ለማመቻቸት ጥረት እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። ይህ ህገ ወጥ ቡድን በትግራይ ሕዝብ ላይ እያደረሰ የሚገኘው ከፍተኛ ሰብዓዊ በደልም በተለያዩ ሀገራትና በዓለም አቀፍ ተቋማት ጭምር እየተወገዘ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ቡድኑ "ፅምዶ" በሚል ስያሜ ከሻዕቢያ፣ ከሱዳንና ከሀገር ውስጥ ፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ጥምረት በመፍጠር፣ ኢትዮጵያን እያተራመሰ ለመኖር አልሞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አንስተዋል። የትግራይ ክልል እናቶች በፅንፈኛው የሕወሓት ቡድን ላይ ድንጋይ እየወረወሩ ነው ያሉት ወይዘሮ ኬሪያ፤ የክልሉ ወጣትና ሕዝብም የቡድኑን እኩይ ሴራ በስፋት እየታገለ መሆኑን አስረድተዋል። ከሻዕቢያ ጋር ከሚፈጽመው የወርቅና የከበሩ ማዕድናት ምዝበራ ባሻገር፣ የትግራይ ወጣቶችን ለሱዳን ጦርነት በመሸጥ የውጭ ምንዛሬ ገቢን የጦር መሣሪያ መግዣ እያደረገ መሆኑን አጋልጠዋል። በተጨማሪም በፍጹም ጭካኔ ሕፃናትን ከእናት ጉያ በመንጠቅና ወደ ጦር ካምፕ በማጋዝ፣ በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ የሕግ ድንጋጌ የሚያስጠይቅ ሰብዓዊ ግፍ እየፈጸመ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ተቋማትና ዜጎች የሚደርስበትን ውግዘት ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት፣ የክልሉን ሕዝብ ወደ ባሰ ጥፋት እየመራው ይገኛል ብለዋል። የሀገር ሽማግሌዎች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማትና ሀገራት የቡድኑን እኩይ ሴራ ሊታገሉት እንደሚገባ ተናግረዋል። የክልሉን ትምህርት ቤቶችም አስቀድሞ በመዝጋትና ወጣቱን ወደ ጦር ካምፕ በማጋዝ የትግራይን ተተኪ ትውልድ እያመከነ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናንም "እራሴ አዘጋጃለሁ" በሚል፣ የወጣቱን የነገ ተስፋና ሕልም እያጨለመ መሆኑን አንስተዋል። ይህም ቡድኑ ሆን ብሎ የትግራይ ክልልን ተተኪ ትውልድ በመዋቅር እያጠፋ እንደሚገኝ ማሳያ ነው ብለዋል።
የመንግስት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ግጭትን በዘላቂነት ለማስቆምና ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ቁርጠኝነቱን የሚያሳይ ነው
Jul 9, 2026 650
ገንዳውኃ፣ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፡- የመንግስት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ግጭትን በዘላቂነት ለማስቆምና ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ቁርጠኝነቱን የሚያሳይ መሆኑን በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳውሃ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር በሰጡት ማብራሪያ መንግስት ችግሮችን በውይይት ለመፍታት የተያዘውን ጠንካራ አቋም መግለፃቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ለዘላቂ ሰላም፣ ለንግግርና ውይይት መንግስት ሁል ጊዜም ዝግጁ መሆኑን አንስተው የግጭትና ጦርነት እሳቤ አውዳሚና ትርፍ የሌለው ስለመሆኑ ተናግረዋል። በመሆኑም የመንግስት የሰላም በር ሁልጊዜም ክፍት መሆኑን ገልጸው ሰላምን ለሚመርጡ ሁሉ ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጠዋል። በአማራ ክልል ምእራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውሃ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች የመንግስት የሰላም ጥረትና ቁርጠኝነት የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩም ማብራሪያ መንግስት ለሰላም ያለውን ጠንካራ አቋምና በጥፋት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ውለው ሳያድሩ እንዲመለሱ እድል የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወይዘሮ ትግስት እማኘው፣ ወጣት ገብረኪዳን መንጋው እና አቶ ኪሩቤል መንግስቴ፤ የመንግስት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ግጭትን በዘላቂነት ለማስቆምና ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ቁርጠኝነቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። በተለይም በአማራ ክልል ህዝቡ ዘላቂ ሰላምና ልማት ይፈልጋል ያሉት ነዋሪዎቹ መንግስት ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት የተረጋጋች ሀገር ለመገንባት የሚያደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። የመንግስት የሰላም ጥረት የሀገርና የህዝብ አንድነት ለማጠናከር፣ ሰላምን ለማስፈንና ልማትን ለማፋጠን መሰረት የሚያኖር መሆኑን ነው የተናገሩት። የመንግስትን የሰላም ጥረት በማገዝና በመደገፍ አካባቢያውን ከጸረ ሰላም ቡድኖች ለመጠበቅ የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ያለው የሰብዓዊ መብት ረገጣ ተባብሶ ቀጥሏል-ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት
Jul 9, 2026 753
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- ህገ-ወጡ የህወሃት ቡድን የሰላም ስምምነቱን በማፍረስ በትግራይ ክልል የሰብዓዊ መብት ረገጣውን እያባባሰ መምጣቱን የመጀመሪያው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ የነበሩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ገለጹ፡፡ የመጀመሪያው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ የነበሩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ወቅታዊውን የትግራይ ክልል ሁኔታ አስመልክቶ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች ሁለንተናዊ እድላቸው እየጠበበና በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እየገቡ ነው። ቡድኑ ወጣቶችን በተለያየ መልክ ለጦርነት መማገጃነትና ለውክልና ጦርነት እየተጠቀመባቸው እንደሚገኝም አጋልጠዋል። የሰብዓዊ መብት ረገጣው ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ እጅግ እየከፋና ጫፍ ላይ መድረሱንም ገልፀው፤ በርካታ ወጣቶች በግድ እየታፈሱ ወደ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየተወሰዱ መሆኑን አስረድተዋል። ከዚህም አልፎ ወደ አዲስ አበባ ለመውጣት የሚሞክሩ ተጓዦችን ጭምር በየመንገዱ ከነበሩበት ተሽከርካሪ እያስወረዱ ወደ ስልጠና የሚወስዱበት፣የሚያስሩበትና እስከ ሞት ቅጣት የሚደርስ እርምጃ የሚፈጽሙበት ሁኔታ መኖሩን ጠቅሰዋል። የቡድኑን ፍላጎት የማይቀበሉ በርካታ ወላጆችም በየአካባቢው ለእስር እየተዳረጉ ይገኛሉ ሲሉ ተናግረዋል። ታጣቂዎች ወጣቶች ትምህርታቸውን በግድ እንዲያቋርጡ በማድረግ በካምፕ ውስጥ በማሰልጠን ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በዚህም ምክንያት በትግራይ ክልል ውስጥ መደበኛ የልማትና የዴሞክራሲ እንቅስቃሴ ጠፍቶ ህዝቡ ወደ ውጭ ሀገራት እንዲሰደድ እየተገደደ ነው ብለዋል። ይህ ህዝብን አሸብሮና አስገድዶ ወታደር የማድረግ ዓላማ ከሻዕቢያ የተኮረጀና የተማሩት ትምህርት ነው ያሉት ፕሮፌሰር ክንደያ፤በአሁኑ ወቅት ድርጊቱ በፍጥነትና በስፋት እየተገበረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በትግራይ ህዝብ ዘንድ ስለ ሰላምና ዴሞክራሲ ሳይሆን ስለ ራሱ ህልውና ብቻ የሚጠይቅበት አስገዳጅ ሁኔታ መፈጠሩን ጠቁመዋል። ይህ በትግራይ ክልል ውስጥ ችግር እየፈጠረ ያለው ቡድን በአስቸኳይ ተጠያቂ የሚሆንበት አሰራር ሊዘረጋ እንደሚገባ ፕሮፌሰሩ አሳስበዋል። መገናኛ ብዙሃን ሰላም እንዲመጣ በትግራይ ክልል ያለውን እውነተኛ ጥፋት ለህዝብ በማጋለጥ በቁርጠኝነት መስራትና መታገል ይኖርባቸዋል ሲሉ አስገንዝበዋል።
መንግሥት ለታጠቁ ኃይሎች የሚያቀርበው ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ለሀገር ዘላቂ ሰላም ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው
Jul 9, 2026 675
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦መንግሥት ለታጠቁ ኃይሎች የሚያቀርበው ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ለሀገር ዘላቂ ሰላም ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ መሆኑን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግስት ለዘላቂ ሰላም፣ ለንግግርና ውይይት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን አስረድተዋል። የግጭትና የጦርነት እሳቤ አውዳሚና ትርፍ የሌለው መሆኑን በአሁኑ ወቅት ለሀገር የሚያስፈልገው ሰላም፣ ትብብርና አብሮነት መሆኑን በማብራሪያቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። መንግሥት ዛሬም ቢሆን በጫካ ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች ጋር ለመወያየትና ለሰላም ያለው በር ክፍት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰጡት ማብራሪያ ተከትሎ ኢዜአ ያነጋገርናቸው የመዲናዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ መንግስት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ የሚያደርገው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡ ከነዋሪዎች መካከል ተስፋዬ ጸጋዬ እንዳሉት፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰላም ዙሪያ የሰጡት ማብራሪያ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ያለውን ጽኑ አቋም ያሳየበት ነው። መንግሥት በጫካ ለሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎች በተደጋጋሚ የሚያቀርበውን የሰላም ጥሪ ለአብነት አንስተዋል። በመሆኑም የታጠቁ ኃይሎች ይህንን የመንግሥት ጥሪ በአዎንታ በመቀበል ለዘላቂ ሰላምና ልማት የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተመሳሳይ አቶ ፍቃዱ ንጉሤ፤ የግጭትና የጦርነት እሳቤ አውዳሚና ትርፍ የሌለው መሆኑን በመገንዘብ፣ የታጠቁ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ መቀበል እንዳለባቸው አስታውቀዋል። በልማት የተገኘውን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ ዘላቂ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ለሁለንተናዊ ዕድገትና ለጋራ ተጠቃሚነት መሥራት እንደሚገባ የገለጹት ደግሞ አቶ አስናቀ ለጪሳ ናቸው። የታጠቁ ኃይሎች መንግሥት ለሰላም የከፈተውን በር በአግባቡ በመጠቀም ለአገር ልማትና ብልጽግና በትጋት መሥራት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
በጠመንጃ አፈሙዝ ስልጣን ለመያዝ መሞከር ጊዜው ያለፈበት ኋላ ቀር እሳቤ ነው-የአብን ምክትል ሊቀመንበር
Jul 9, 2026 810
ባህር ዳር፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በጠመንጃ አፈሙዝ ስልጣን ለመያዝ መሞከር ጊዜው ያለፈበት ኋላ ቀር እሳቤ መሆኑን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ምክትል ሊቀመንበር መልካሙ ፀጋዬ ገለጹ። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ስርአት ተለውጦ አካታችና አሳታፊ በመሆኑ በሀገሩ ጉዳይ ላይ ሁሉም በእኩልነት የሚሳተፍበት ምቹ የፖለቲካ ምህዳር ተፈጥሯል። በኢትዮጵያ አጋር ተብለው የዳር ተመልካች የነበሩ ክልሎች አሁን ላይ እኩል ተሳታፊ ሆነው በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እየወሰኑ ነው። በውጭና በሀር ውስጥ መሰረታቸውን አድርገው በትጥቅ ትግል ውስጥ የነበሩ ወገኖችም የለውጡ መንግስት የፈጠረውን ምቹ መደላድል ተጠቅመው በሰላማዊ ትግል ቀጥለዋል። የፖለቲካ ስርአቱ በዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት እየዳበረ በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባት ስራም በመከናወን ላይ ይገኛል። እነዚህን መልካም እድሎች በመግፋት በጠመንጃ ለጥያቄያችን መልስ እናገኛለን፤ አሸንፈንም ስልጣን እንይዛለን በማለት በጫካ የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኞች ይስተዋላሉ። በመሆኑም በዚህ ዘመን በኢትዮጵያ ከሰላማዊ የትግል ስልት ውጭ የትኛውም አይነት የሀይል እንቅስቃሴ አክሳሪና የማያዋጣ መሆኑን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ምክትል ሊቀመንበር መልካሙ ፀጋዬ ገልጸዋል። በዚህ ዘመን በምክክር ችግሮችን የመፍታት እና በምርጫ ተወዳድሮ የማሸነፍ ሰፊ እድል እያለ በጫካ የሚደረግ የጠመንጃ እንቅስቃሴ በፍፁም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ፓርቲያችን በፅኑ ያምናል ብለዋል። በኢትዮጵያ በጠመንጃ ስልጣን ለመያዝ መሞከር ጊዜው ያለፈበት ኋላ ቀር እሳቤ በመሆኑንም ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የሃይል አማራጮችን በመተው በመቀራረብ በምክክር የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሁላችንም ዝግጁነትና ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ብለዋል። በተቃርኖ የከረሩ ዋልታ ረገጥ እሳቤዎችን በማለዘብ በምክክር ወደ መሀል በማምጣት ለችግሮቻችን ዘላቂ መፍትሄ ልናበጅ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘውን ሀገራዊ የምክክር እድል መጠቀም የትውልድንና የሀገርን ቀጣይ እጣ ፋንታ መወሰን ይገባናል ብለዋል። በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የተለዩ አጀንዳዎች የዜጎችን የዘመናት ጥያቄዎች ጭምር ማእከል ያደረጉ በመሆኑ ለስኬታማነቱ መስራት የሁላችንም ሃላፊነት ነው ሲሉ አቶ መልካሙ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ሃሳብ ለማካተት ጥረት የተደረገበት መሆኑን አንስተው እድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ማለታቸው ይታወሳል።
ማህበራዊ
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሚያከናውኗቸው ተግባራት የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ሊያጎለብቱ ይገባል
Jul 9, 2026 682
ሰመራ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሚያከናውኗቸው ተግባራት የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አመለከተ። በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በአፈፃፀም ሪፖርትና በቅንጅታዊ ተግባራት ዕቅድ ላይ በሰመራ ከተማ ውይይት አድርገዋል። በወቅቱም የአፋር ክልል ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደረሳ መሐመድ እንደገለፁት፤ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚያከናውኗቸው ተግባራት የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ሊያጎለብቱ ይገባል። ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ ድርጅቶቹ እርስ በርስ ተናበውና ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ አመልክተዋል። ባለፈው በጀት ዓመት በክልሉ ድርጅቶቹ 60 ዋና ዋና ፕሮጀክቶችን ያከናወኑ መሆኑን ገልጸው ለፕሮጀክቶቹም በአጠቃላይ 6 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉን አስረድተዋል። ከፕሮጀክቶቹ መካከል 18ቱ በጤናና በሥነ-ምግብ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን አብራርተዋል። ድርጅቶቹ በሚያከናውኗቸው የልማት ሥራዎች የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጨባጭ ፍላጎት ከማገናዘብ ባለፈ የሥራ ዕድሎችን ማመቻቸት እንደሚገባቸውም ምክትል ኃላፊው አመልክተዋል። በክልሉ በተከናወኑ የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች ዘርፎች ድርጅቶቹ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ጉልህ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንኑ ኅብረተሰብን ማዕከል ያደረገ ድጋፋቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም አሳስበዋል። የ"ፍሬንድሺፕ ሰፖርት አሶሴሽን" ፕሮግራም ማናጀር ወይዘሮ የማ ዳንኤል በበኩላቸው፤ ፕሮግራሙ በጤና፣ በውሃና በሰላም ግንባታ ዘርፎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማላቅ በትጋት እንደሚሰሩም ተናግረዋል። በክልሉ በተለያዩ ወረዳዎች በሕዝብና እንስሳት ጤና ዘርፎች እንዲሁም በውሃ ላይ በመሰማራት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ያጎለበቱ በርካታ ተግባራትን እንዳከናወኑ የገለጹት ደግሞ "ኮፕ" (COOP) በተሰኘው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት የአፋር ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ መሐመድ ጎንፍሬ ናቸው። በበጀት ዓመቱ ድርጅቶቹ በክልሉ በሚገኙ ስድስት ዞኖች ውስጥ በስፋት ተሰማርተው፣ ማኅበረሰብ ተኮር የሆኑ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በስኬት ማከናወናቸውም ተገልጿል።
የሃይማኖት ተቋማት ለአገር ሰላምና አብሮነት የጀመሩትን ተቀራርቦ የመሥራት በጎ ልምድ ሊያጠናክሩ ይገባል
Jul 9, 2026 514
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2 /2018(ኢዜአ) ፦ የሃይማኖት ተቋማት ለአገር ሰላምና አብሮነት የጀመሩትን ተቀራርቦ የመሥራት በጎ ልምድ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ኸይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) አመለከቱ። የሰላም ሚኒስቴር በህዝቦች መካከል አብሮነትን ማጠናከርና ዘላቂ ሰላም ግንባታን በተመለከተ ከሃይማኖት ተቋማት መሪዎች እና ተወካዮች ጋር ውይይት አካሂዷል። ሚኒስትር ዴኤታው በወቅቱ እንዳሉት፤ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተሰጠውን ተልዕኮ መነሻ በማድረግ እንዲሁም የሃይማኖት ተቋማት ለሰላም ግንባታና ለብሔራዊ መግባባት ያላቸውን አይተኬ ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት በቅርበት እየሠራ ይገኛል። ይህ ዓይነቱ ትብብርም የሃይማኖት አባቶች በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ በመቅረጽ ረገድ የጎላ ድርሻ እንዲወጡና የሕዝቦችን ሰላምና አብሮነት እንዲያጎለብቱ ለማስቻል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል። መንግሥት የሃይማኖት በዓላት በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ በትኩረት እየሠራ እንደሚገኝም ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል። ይህንን ሂደት ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግም በትኩረት እንደሚሠራም አክለው ተናግረዋል። መንግሥት ከሃይማኖት ተቋማት ጋር ያለው ግንኙነት ሰላማዊ፣ በመከባበር ላይ የተመሠረተና ሕገ-መንግሥታዊ የሃይማኖትና የመንግሥትን መለያየት መርህ የጠበቀ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። በተቋማቱ መካከል ያለው ሰላምና መልካም ግንኙነት መሻሻሉን ጠቁመው፤ አንዱ ተቋም ከሌላው ጋር በአብሮነትና መደጋገፍ ችግሮቹን ለመፍታት የሚያሳየው አጋርነት እያደገ መምጣቱ የሚበረታታና የሚያስመሰግን መሆኑንም ነው የገለጹት። ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ለተከታዮቻቸው በአብሮነት፣ በጋራ ተከባብሮ መኖር እና በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የጀመሩትን ተቀራርቦ የመስራት በጎ ልምድ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አስተላልፈዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሃይማኖት መሪዎች በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ሀሳባቸውን አንስተዋል። ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት መሥራታቸው በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመንቀሳቀስ ዕድል መፍጠሩን ገልጸው ይህንን በጎ ሂደት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ መናገራቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የመንግሥት አዲሱ የቤት ልማት ዕቅድ ለዜጎች ትልቅ እፎይታ የሚሰጥ ነው
Jul 9, 2026 201
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):-መንግሥት በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ በመላ ሀገሪቱ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት ማቀዱ ለዜጎች ትልቅ እፎይታን የሚሰጥ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው፤ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ ሰፊ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው፣ የቤት ልማት ጉዳይ ከጉባ ብስራቶች መካከል አንዱ መሆኑንና መንግሥት በከፍተኛ ትኩረት እንደሚሠራበት ተናግረዋል። በዚህም መሠረት ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ ብቻ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣዮቹ አምስት ዓመታትም 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶችን በመንግሥት፣ በግል၊ በመንግሥትና በግል አጋርነት እንዲሁም በሌሎች አማራጮች ለመገንባት ዕቅድ ተይዞ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህንን ስኬታማ ማድረግ የሚያስችል አዲስ የመኖሪያ ቤት ፖሊሲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ግንባታውን በገጠርና በከተማ ለማፋጠን በትጋት እየተሠራ መሆኑን አስረድተዋል። በቴክኖሎጂ የታገዘ የግንባታ ፍጥነትን ለመጨመርም እንደ 3ዲ ያሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ወደ ሥራ እየገቡ መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቤት ልማት ዙሪያ የሰጡትን ማብራሪያ በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳመለከቱት፤ ይፋ የተደረገው የቤት ልማት ሥራ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት ነዋሪዎች መካከል አቶ ተሾመ ረጎ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት ነዋሪዎችን እየፈተነ ያለው የመኖሪያ የቤት አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ምላሽ ሊያገኝ ይገባል፡፡ መንግሥት ይህንን ችግር ለመቅረፍ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሰጠው ትኩረትና ያከናወናቸው ተግባራት በርካታ ዜጎችን የቤት ባለቤት ማድረግ የቻለ ቢሆንም፣ አሁንም ቢሆን የችግሩ ስፋት ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምክር ቤቱ ያደረጉት ንግግር መንግሥት የቤት ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት ያለውን ቁርጠኝነት ይበልጥ ያረጋገጠ በመሆኑ ለነዋሪው ትልቅ ተስፋ የሰጠ ነው ብለዋል። ሌላኛው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ መጋቢ ሥርዓት አበራ ግሩም በበኩላቸው፤ አዲስ አበባ የሀገሪቱ ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን ሰፊ የቤት ልማት ግንባታ እንደሚያስፈልጋት ጠቁመዋል። ይህንን ችግር ለመቅረፍ መንግሥት ልዩ ትኩረት መስጠቱ እንዳስደሰታቸው ገልጸው፤ በቀጣይ ሊገነቡ የታሰቡት ቤቶች ለመንግሥት ሠራተኛውና ዝቅተኛ ገቢ ላለው የሕብረተሰብ ክፍል ትልቅ እፎይታ የሚሰጡ በመሆናቸው ግንባታው ሊፋጠን እንደሚገባ ተናግረዋል። የመዲናዋ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ዝናሽ ተሰማ በበኩላቸው፤ አሁን ያለውን ነባራዊ የመኖሪያ ቤት እጥረት ለመቅረፍ የታቀደው ይህ የቤት ልማት ዕቅድ ለከተማዋ ነዋሪዎች ትልቅ እፎይታ የሚሰጥና የሚያስደስት መሆኑን ተናግረዋል። መንግሥት በቀጣይ ያቀደው ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ቤቶች ግንባታ እጅግ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ አቶ ማስረሻ አፈወርቅ ናቸው። የቤት ልማቱ ተደራሽነትና ቀጣይነት እንዲኖረው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስታውቀዋል።
አዲሱ ስትራቴጂክ ዕቅድ የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ተልዕኳችንን በገለልተኝነትና በተጠያቂነት ለማከናወን ዳግም ቃል የምንገባበት ነው
Jul 9, 2026 585
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2 /2018(ኢዜአ)፦ አዲሱ ስትራቴጂክ ዕቅድ የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ተልዕኳችንን በገለልተኝነትና በተጠያቂነት ለማከናወን ዳግም ቃል የምንገባበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራበትን ስትራቴጂክ ዕቅድ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በዚሁ ወቅት፤ ኮሚሽኑ በአዋጅ የተሰጠውን ሰብዓዊ መብቶችን የማስጠበቅ፣የማስፋፋትና የመከታተል ሥልጣንና ኃላፊነት በተሟላ ሁኔታ ለመወጣት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰብዓዊ መብቶች የተጠበቁ፣ የተከበሩና የተሟሉ እንዲሆኑ ለማድረግ ባከናወናቸው ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን በተደረገ ግምገማ ማረጋገጥ መቻሉን ተናግረዋል። ኮሚሽኑ ከዚህ በፊት ይመራበት የነበረው ስትራቴጂክ ዕቅድ የትግበራ ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ፣ አዲሱ ስትራቴጂክ ዕቅድ ይፋ መደረጉንም አብራርተዋል። ይህ ስትራቴጂክ ዕቅድ በርካታ አዳዲስ የለውጥ ሐሳቦችን እንዳካተተ በመጠቆም፤ከዚህ በፊት ከነበረው በበለጠ ሁኔታ የሚወጡ ሕጎችና ፖሊሲዎች ሰብዓዊ መብቶችን ያከበሩና የተጣጣሙ እንዲሆኑ ትኩረት ማድረጉን ገልጸዋል። ዜጎች ከልጅነታቸው ጀምሮ ስለ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ግንዛቤ ይዘው እንዲያድጉ ለማድረግም፣የሰብዓዊ መብቶች ትምህርትን በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ ለማካተት እንደሚሠራም ጠቁመዋል። በተጨማሪም በሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ላይ የሚሠራ የጥናትና ምርምር ክፍል እንዲሁም ኢንስቲትዩት ለማቋቋም መታቀዱን ዋና ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። ለዚህም ተግባራዊነት ኮሚሽኑ ከባለድርሻ አካላትና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል መስፍን እርካቤ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን ተቀብላ ያጸደቀች ሀገር ናት ብለዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት ቋሚ ኮሚቴው ባደረገው ክትትል ኮሚሽኑ ተጨባጭ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ሥራዎችን ማከናወን መቻሉን ማረጋገጥ ተችሏል ነው ያሉት። በሴቶችና ህጻናት መብቶች፤ በህግ ታራሚዎች አያያዝ፣ በስደተኞች አያያዝ፣ በአካል ጉዳተኞች መብት አጠባበቅ ዙሪያ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን አመላክተዋል። አዲሱ ስትራቴጂክ እቅድ ኮሚሽኑ ስራውን ለማላቅ የሚያስችለው መሆኑን ጠቁመው፤ ቋሚ ኮሚቴው ለስትራቴጅክ እቅዱ መሳካት ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። ስትራቴጂክ ዕቅዱ ሰብዓዊ መብቶችን ይበልጥ ለማስጠበቅና የፍትሕ ተደራሽነትን ለማስፋት አይነተኛ ሚና እንዳለው የገለጹት ደግሞ የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተወካይ ነብይ ተካ ከበደ ናቸው፡፡ ለእቅዱ ተግባራዊነት ሃይማኖት ተቋማት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
ኢኮኖሚ
ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ቀጣናዊ ግቦች እንዲሳኩ ከአባል ሀገራት ጋር በትብብር መስራቷን ታጠናክራለች
Jul 9, 2026 709
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ቀጣናዊ ግቦች እንዲሳኩ ከአባል ሀገራት ጋር በትብብር መስራቷን እንደምታጠናክር የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር 22ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያውን ወደ ሥራ ለማስገባትና የትስስሩን ተቋማዊ እድገት ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ጠቅሰዋል። ትስስሩን ለመምራት ኢትዮጵያ በሊቀ-መንበርነት መመረጧን አስታውሰው፤ የተጀመሩ ቀጣናዊ ጥረቶችን ለማስቀጠል ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ የትስስሩን በተቋማዊ ታማኝነት፣ በቀጣናዊ አንድነትና በሕግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ የተቀናጀ ገበያ የመፍጠር የጋራ ግብን ለማሳካት ከሁሉም አባል ሀገራት ጋር ትብብሯን እንደምታጠናክር አመልክተዋል። የጋራ ቁርጠኝነትን በማጉላት፣ ለአባል ሀገሮች ሁሉ ጥቅም ሲባል ድርጅታችንንም ሆነ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያችንን ለማጠናከር የተገኘውን መልካም አጋጣሚ ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ደኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ሱዳን ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ሚናዋን እየተወጣች ነው ብለዋል። በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ማዕቀፍም ቀጣናውን በኃይል የማስተሳሰር ሚናዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ በአባል ሀገራቱ መካከል በጋራ ለመስራት የተደረሱ ስምምነቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ውሎችን ጨምሮ በተለያዩ አሰራሮች ላይ ውይይት ተደርጎ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል። በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ገበያ ማዕከሉ ቦታ ለመወሰን ሌላው የጉባኤው ዋና የውይይት አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር 13 ሀገራትን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን፤ በአባል ሀገራቱ መካከል የኤሌክትሪክ ኃይልን በጋራ ለመጠቀም፣ የኃይል ግብይት ለማካሄድ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ታልሞ የተመሠረተ ነው። ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛንያ፣ ኡጋንዳ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊያና ሊቢያ የትስስሩ አባል ሀገራት ናቸው።
የጉምሩክ ኮሚሽን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ738 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ
Jul 9, 2026 589
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 738 ነጥብ 14 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) ገለፁ። የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) የተጠናቀቀውን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ክንውን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ በበጀት ዓመቱ 725 ነጥብ 27 ቢሊዮን ብር ለማግኘት አቅዶ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል ብለዋል። በዚህም በተከናወኑ ውጤታማ ሥራዎች 738 ነጥብ 14 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታውቀዋል። የተገኘው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ77 ነጥብ 56 በመቶ ብልጫ ያስመዘገበ እንደሆነ አመላክተዋል። ኮሚሽኑ ሀገሪቱ ከቀረጥና ታክስ ተገቢውን ገቢ እንድታገኝ በማድረግ፣ የኮንትሮባንድና ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከልና በመቆጣጠር እንዲሁም የወጪ ንግድ እንዲሳለጥ የሚጠበቅበትን ሚና መወጣቱንም ጠቁመዋል። የተሰበሰበው ገቢ ከወጪ ንግድ ቀረጥና ታክስ፣ በወጪ ንግድ ላይ ከሚስተዋል የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ እንዲሁም ከሌሎች ኮሚሽኑ ካከናወናቸው ተግባራት የተገኘ መሆኑን አብራርተዋል። የመንግሥት የፖሊሲ አቅጣጫዎች ለዘርፉ የተመቹ መሆን፣ የተደረጉ ተቋማዊ የሪፎርም ሥራዎች እና አሠራርን በቴክኖሎጂ የማዘመን ተግባራት ለገቢው ማደግ አቅም መፍጠራቸውን ገልጸዋል። የጉምሩክ ኮሚሽን በ2019 የበጀት ዓመት ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱንም አስታውቀዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሕገወጥ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን የመቆጣጠር ሥራን በማጠናከር፥ ከዘርፉ ጥቅም ማስገኘት ያስቻሉ ውጤታማ ሥራዎች መሰራታቸውን አስገንዝበዋል። በገቢና በወጪ እቃዎች ላይ በተሰራው የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን የመከላከል ሥራም 28 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር የሚገመቱ ምርቶች መያዛቸውንም አብራርተዋል። በኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ላይ በተደረገ ቁጥጥር ከተያዙ ምርቶች መካከል ኤሌክትሮኒክስ፣ መድሃኒት፣ አደንዛዥ እጽ፣ የቁም እንስሳት እና ሌሎች እንደሚገኙበት አመላክተዋል። አሁንም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እያሳደረ ያለውን የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል
Jul 9, 2026 223
መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞን የዳሪሙ ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሩዝ ልማት ስራ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣና አገሪቱ በምግብ ራሷን ለመቻል በምታደርገው ጥረት ውስጥ እንደ አዲስ ስትራቴጂካዊ ሰብል እየታየ ያለ ነው። መንግስት በአሁኑ ወቅት በተለያዩ አካባቢዎች ለሩዝ ልማት ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም እና በዘርፉ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከውጭ የሚገባውን ምርት ለመተካት ሰፊ ትኩረት ሰጥቷል ። በዞኑ የዳሪሙ ወረዳ ቤና 3 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ኑረዲን ኡስማን፣ አህመድ ሁሴን እና ኢብሳ አሊዩ ለኢዜአ እንዳሉት ፤በኩታ ገጠም ሩዝን በማልማት በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው አድጓል። በተለይ ሜካናይዝድ በሆነ መንገድ የሩዝ ልማቱን በትራክተር እና በኩታ ገጠም እርሻ ለማልማት መቻሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንዳገዛቸው ነው የገለጹት። ለሩዝ ልማት ስራ ትኩረት በመሰጠቱና ከራሳችን አልፎ ለገበያ የሚቀርብ ምርት በማስገኘቱ በተሻለ መንገድ ተጠቃሚ ለመሆን አስችሎናል ብለዋል። በቀጣይ ጊዜያትም የሩዝ ልማት ስራውን ከፍ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን አርሶ አደሮቹ ተናግረዋል። የዳሪሙ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታሪኩ ኢታና በበኩላቸው፤ በወረዳው የመኽር እርሻ 128 ሺ ሔክታር መሬት ላይ ሩዝን በማልማት ከ4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል። በሩዝ ልማቱ ከ172 ሺ በላይ አርሶ አደሮች የሚሳተፉ ሲሆን ከ56 ሺህ ኩንታል በላይ የምርት ማሳደጊያ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ እንደሚውልም ገልጸዋል። የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳሙ ታከለ በበኩላቸው፤ በዞኑ የግብርና ልማትን ስኬታማ ለማድረግ አርሶ አደሩ በወቅቱ ግብአት እንዲቀርብለት ከማድረግ ባለፈ አርሶአደሮች የባለሙያዎች ድጋፍ እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል። በመኽሩ ወቅት በሚካሔደው የሩዝ ልማት ስራ 230 ሺ ሔክታር መሬት በማልማት ከ9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን አንስተዋል ።
በሀረሪ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል
Jul 9, 2026 204
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በ2018 በጀት አመት ከ4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ያሲን አብዱላሂ ገልጸዋል። ኃላፊው እንደተናገሩት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚታቀዱ ፕሮጀክቶች እውን እንዲሆኑ በተለይም ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ ነው። በመሆኑም በተጠናቀቀው በጀት አመት የክልሉን ገቢ አሟጦ ከመሰብሰብ አንፃር ዘርፈ ብዙ ርብርብ ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰዋል። በዚህም በአመቱ 4 ቢሊየን 672 ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ4 ቢሊየን 625 ሚሊየን ብር በላይ በመሰብሰብ፣ የእቅዱን 99 በመቶ ማሳካት መቻሉን ጠቁመዋል። ከተሰበሰበው ገቢ መካከልም በቀጥታ ታክስ ከ2 ቢሊየን 612 ሚሊየን ብር በላይ፣ ቀጥታ ካልሆነ ታክስ 2 ቢሊየን 211 ሚሊየን ብር፣ ታክስ ነክ ካልሆነ ገቢ ደግሞ ከ275 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ጠቁመዋል። እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ደግሞ ከ526 ሚሊየን ብር በላይ የተሰበሰበ መሆኑን ተናግረዋል። ገቢው ከ2017 ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነፃፀርም ከ1 ቢሊየን 516 ሚሊዮን በላይ ብልጫ እንዳለውም ነው የገለጹት። በተለይም የውስጥ መናበብን በማሳደግና ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት፤ አገልግሎት አሰጣጥን በማሳደግ፤ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራርን መዘርጋቱ፤ ውዝፍ እዳን አሟጦ መሰብሰቡ እና የቅሬታ አፈታት ስርዓትን ማሻሻል ለገቢ አሰባሰቡ መሻሻል እገዛ አንዳደረገ አስረድተዋል። የታክስ ተደራሽነት ማስፋትና ብቃትና ተጠያቂነትን መሠረት ያደረገ የሰው ኃይል ስምሪትና አመራር መተግበር መቻሉም ሌላው ለገቢው ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ጉዳይ መሆኑን ጠቁመዋል። የአሰራር ስርዓት ላይ የነበሩ መመሪያዎችን በማሻሻል እና ህገ-ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊነት የመቀየር ስራ በትኩረት መሰራቱ በዓመቱ የታቀደው እቅድ እንዲሳካ አስችሏል ብለዋል። በ2019 የበጀት በጀት ዓመትም ከግብር ከፋዩና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ እና ለተጀመረው ክልላዊና ሀገራዊ የብልፅግና ጉዞ በብቃት ኃላፊነትን ለመወጣት ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑም አንስተዋል። በዓመቱ የተከናወነው የገቢ አሰባሰብ እንዲጎለብት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በተለይም ለታማኝ ግብር ከፋዮች፣ የተቋሙ ሰራተኞች፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የቢሮው ኃላፊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ያመጣ ትውልድ ተሻጋሪ ድንቅ ሥራ ነው
Jul 9, 2026 804
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):-መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ያመጣ ትውልድ ተሻጋሪ ድንቅ ሥራ ነው ሲሉ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ገለጹ። የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የመንግሥት አገልግሎትን ማሻሻል ለሁለንተናዊ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ይህንንም ተከትሎ መንግሥት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የመንግሥት አገልግሎትን ለማሻሻልና ውጤታማ ለማድረግ፣ በሲቪል ሰርቪሱ ላይ ያተኮሩ በርካታ የለውጥ ተግባራትን በትኩረት እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በዚህም መሠረት ኮሚሽኑ የሲቪል ሰርቪስ ተቋማትን መገንባት፣ መዋቅርን ማስተካከል፣ በብቃት መቅጠርና ብዝሃነትን ያረጋገጠ የሲቪል ሰርቪስ መፍጠርን ቀዳሚ እርምጃዎች አድርጎ ሲሠራባቸው መቆየቱን ጠቁመዋል። ከእነዚህ የለውጥ ተግባራት መካከል የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ውጤታማ ለማድረግ በቅርቡ ተግባራዊ የተደረገው የ"አንድ መሶብ" አገልግሎት መዋቅር በዋነኝነት የሚጠቀስ መሆኑን ኮሚሽነሩ አንስተዋል። የባለብዙ አገልግሎት ማዕከል የሆነው የአንድ መሶብ አገልግሎት ከሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች 106 የመሶብ ማዕከላት መከፈታቸውን አስታውቀዋል። ከእነዚህ በተጨማሪ ሦስት ተንቀሳቃሽ ማዕከላት እና የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ የተሰኘ የሞባይል አፕሊኬሽን ወደ ሥራ መግባታቸውን ተናግረዋል። እነኚህ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለማኅበረሰቡ ፈጣንና ውጤታማ የሆነ አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ እነዚህ አሠራሮች ወደ ሥራ መግባታቸውን ተከትሎ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን የገለጹት ኮሚሽነሩ፤ ሥርዓቱ ዜጎች ያለ ምንም እንግልት አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል በመፍጠሩ በተቋማት ላይ ያላቸው እምነት እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። አገልግሎቱ መሰጠቱን ተከትሎ በተደረገ ዳሰሳ ጥናትም በአሁኑ ወቅት የደንበኞች እርካታ 98 ነጥብ 8 በመቶ መድረስ መቻሉን አስታውቀዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ወጪና ጊዜን ከመቀነስ ባለፈ፣ ሠራተኞች ዜጋን በደስታ የሚያገለግሉበትን መነሳሳት የፈጠረ፣ ኢንቨስትመንትን የሚያስፋፋ በመሆኑ እንደ ትውልድ የሚያኮራ ትልቅ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የፌደራል ተንቀሳቃሽ መሶብ ማዕከል ተገልጋዮች በበኩላቸው የአንድ መሶብ አገልግሎት ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ የተንዛዛ አሠራርን ያስቀረ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። በሻይ ዕረፍት ጊዜዬ ብቻ መጥቼ አምስት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጉዳዬን ማጠናቀቅ ችያለሁ በማለት የአሠራሩን ቀልጣፋነት ያረጋገጡት አቶ መስፍን ተርፋ ናቸው። አስተያየት ሰጪ አስቻለው ጓዴ በበኩላቸው ቀደም ሲል ከተቋም ወደ ተቋም እየተንከራተቱ የሚያገኙት አገልግሎት አሁን በአንድ ማዕከል ማግኘት መቻላቸው ትልቅ እፎይታ እንደሰጣቸው አስታውቀዋል። ሌላኛዋ ተገልጋይ ወርቅነሽ እሸቱ አገልግሎቱ ረጅም ሰንሰለቶችን በማስቀረት ሰዓትን፣ ጉልበትንና አላስፈላጊ ወጪን በመቀነስ በአጭር ጊዜ ጉዳዬን እንድፈጽም አስችሎኛል ብለዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ለተያያዙ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ የሚያስገኝ ነው
Jul 8, 2026 443
ጅማ ፤ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፡- የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ለተያያዙ ችግሮቻችን ዘላቂ መፍትሄ የሚያስገኝ ነው ሲሉ የጅማ ዞን ማና ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። በጅማ ዞን ማና ወረዳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የዞኑና የወረዳው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ። የማና ወረዳ ነዋሪዎች መንግሥት ለማኅበረሰቡ ጥያቄዎች ቅድሚያ በመስጠት እንደ መሶብ ያሉ ማዕከላትን ወደ ሥራ ማስገባቱ የገባውን ቃል በተግባር እየፈጸመ መሆኑን የሚያሳይ ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ የተሰማሩት የወረዳው ነዋሪ አቶ ዛኪር አወል በሰጡት አስተያየት፤ ከዚህ ቀደም ለአንድ ጉዳይ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይባክንባቸው እንደነበር አስታውሰዋል። ዛሬ አገልግሎት የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ይህንን እንግልት እንደሚያስቀርላቸው ተስፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ሌላኛው ነዋሪ አቶ መሐመድኑር ሸምሱ በበኩላቸው፣ ለዘመናት ይመኙት የነበረውን ፈጣን አገልግሎት በማዕከሉ ማግኘት መጀመራቸውን ጠቅሰው፣ አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ የተቀላጠፈ እንዲሁም ጊዜና ገንዘብን የሚቆጥብ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ነዋሪዎቹ የማዕከሉ ስራ መጀመር ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ችግሮቻቸው ዘላቂ መፍትሄ እንደሚያገኙ ተስፋ እንዲሰንቁ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል። የማና ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰመሩዲን አህመድ በበኩላቸው፣ በወረዳው በበጀት ዓመቱ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 32 ፕሮጀክቶች ተገንብተው መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል። ከተገነቡት መሠረተ ልማቶች መካከል ሁለት ድልድዮች፣ የወጣቶች መሥሪያ ሼዶች፣ የአስተዳደር ሕንጻ እንዲሁም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። በማዕከሉ 88 ዓይነት አገልግሎቶች በ9 መስኮቶች እንደሚሰጡ የገለጹት አስተዳዳሪው፣ በወረዳው ከሚገኙ 14 ሴክተሮች ውስጥ 10 የሚሆኑት ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ መደረጉ የተገልጋዩን እርካታ ከፍ እንዳደረገው አብራርተዋል። በዛሬው ዕለት በወረዳው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የ362 አቅመ ደካሞች ቤቶች ግንባታና እድሳት መጀመሩን አንስተዋል። የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ በዞኑ በማኅበረሰቡ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን የሚመልሱ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለነዋሪዎች ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ፣ የመንግሥትንና የዜጎችን ከአላስፈላጊ ወጪ መታደጉን ጠቁመዋል። የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ቀላልና ዲጂታላይዝ በማድረግ የተገልጋዩን እርካታ የማሳደግ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ቲጃኒ አክለዋል። ከመሠረተ ልማት ግንባታዎች በተጨማሪ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የበርካታ አቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በአፍሪካ ቀዳሚና ተወዳዳሪ የሆነ የጥራት ማረጋገጫ ተቋም ተገንብቷል
Jul 8, 2026 485
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀዳሚና ተወዳዳሪ የሆነ የጥራት ማረጋገጫ ተቋም መገንባቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ ገለጹ፡፡ ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ ከ36 ሺህ በላይ የምርት ጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶችን መስጠት መቻሉንም ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ድርጅቱ በተደራጁ የፍተሻ ላቦራቶሪዎቹ አማካኝነት የምርትና የአገልግሎት ጥራት የማረጋገጥ፣ የምርትና የስራ አመራር ሰርተፊኬሽን እንዲሁም የኢንስፔክሽን አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። በዚህም ድርጅቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመቱ ከ36 ሺህ በላይ የምርት ጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶችን መስጠቱን አስታውቀዋል። በበጀት ዓመቱ የተሰጠው የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ5 ሺህ 500 በላይ አገልግሎቶች እድገት ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል። የድርጅቱን ተደራሽነት ለማስፋትና አገልግሎቱን ወደ ክልሎች ተደራሽ ለማድረግ በተሰራው ሰፊ ስራ በድሬዳዋ ከተማ የመጀመሪያ የሆነውን የነዳጅ፣ የምግብና የንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶች ፍተሻ ላቦራቶሪ ስራ ማስጀመሩንም ገልጸዋል። በተጨማሪም በአዳማ ቅርንጫፍ ባለ አምስት ወለል ህንጻ በማስገንባት በምግብ፣ መጠጥና በግብርና ግብዓቶች ላይ ተጨማሪ የፍተሻ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን በደሴና ኮምቦልቻ ያሉ ቅርንጫፎችንም የማዘመን ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል። በምርትና ስራ አመራር ሰርተፊኬሽን ዘርፍ ከ900 በላይ ድርጅቶች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል። ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲገቡ በጅቡቲ ወደብ የጅምላ ጭነት ኢንስፔክሽን አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። መንግስት የምርትና የአገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ የጀመረው ሰፊ የሪፎርም ስራ ለተቋሙ ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህ የተከናወነው የሪፎርም ስራ ኢትዮጵያ ከተቀላቀለችው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና ለመቀላቀል በድርድር ላይ ካለችበት የዓለም ንግድ ድርጅት አንጻር የሀገሪቱን የንግድ ልውውጥና ኢኮኖሚ ለማሳደግ መሆኑን አስረድተዋል። ይህም ጥራታቸውን ያልጠበቁ የውጭ ምርቶች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ለመከላከልና የሀገር ውስጥ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ትልቅ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። በዚህም በአፍሪካ ቀዳሚና ተወዳዳሪ የሆነ የጥራት ማረጋገጫ ተቋም መገንባቱን ዋና ዳይሬክተሯ ጨምረው ተናግረዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ53 ማዕከላት እየተሰጠ ነው
Jul 8, 2026 431
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ወደ 53 ማዕከላት በማስፋፋት፣ ለማህበረሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። በኢትዮጵያ የመንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ይቀርፋል ተብሎ ወደ ስራ የገባው ይህ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በአሁኑ ወቅት በሁሉም ክልሎች እየተስፋፋ ይገኛል። በኦሮሚያ ክልል የተጀመረው ይኸው አገልግሎት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ተደራሽ እየሆነ መምጣቱንና የአገልግሎት አሰጣጡም ፈጣንና ቀልጣፋ መሆኑ ተገልጿል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳምጠው ገመቹ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ ምላሽ ለመስጠት በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል። በቴክኖሎጂ በመታገዝ በአምስት ዋና ዋና ከተሞች የተጀመረውን አሰራር በማስፋፋት፣ አሁን ላይ በክልሉ በሁሉም ዞኖች 53 ማዕከላት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አስረድተዋል። በማዕከላቱ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ጥራት ይበልጥ ለማሻሻልና ተጠቃሚነቱን ለማስፋትም በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በአገልግሎቱ አማካኝነት ህብረተሰቡ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚፈልገውን ጉዳይ ማሳካት ችሏል፤ ይህም ዜጎችን ከእንግልትና ካልተገባ ወጪ ከመታደጉም ባለፈ፣ ጊዜና ጉልበታቸውን በአግባቡ በልማት ስራዎች ላይ እንዲያውሉ አስችሏል ነው ያሉት። ይህ አሰራር በክልሉ የአገልግሎት ዘርፉ ላይ ከፍተኛ መሻሻል እያስገኘ እንደሚገኝ የገለጹት ምክትል ኃላፊው፤ በተለይም አገልግሎቱ በአንድ ማዕከል የተደራጀ፣ ፈጣን፣ ምቹና ግልጽነት ያለው በመሆኑ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴውን በተሻለ ሁኔታ እያነቃቃው መሆኑን አክለዋል። በአገልግሎቱ የህብረተሰቡን እርካታ ጭምር ከፍ ማድርግ መቻሉንና እስካሁንም ከ700 ሺህ በላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን አቶ ዳምጠው ጠቁመዋል። ማዕከላቱ ከዞኖች ባለፈ ወደ ወረዳዎችም ተደራሽ እየሆኑ በመሆኑ፣ በቀጣይ በሁሉም የክልሉ ወረዳዎች አገልግሎቱን ለማድረስ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ከዚህም በተጨማሪ በቀጣይ የዲጂታላይዜሽን አሰራርን ሙሉ በሙሉ እውን በማድረግ፣ ህብረተሰቡ አገልግሎቱን ባለበት ሆኖ በኦንላይን (Online) ማግኘት እንዲችል በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ስፖርት
ፈረንሳይ ሞሮኮን በመርታት ለግማሽ ፍጻሜ አለፈች
Jul 9, 2026 305
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ማለፍ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በቦስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኪሊያን ምባፔ በ60ኛው እና ኡስማን ዴምቤሌ በ65ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ምባፔ በ28ኛው ደቂቃ ፍጹም ቅጣት ምት ስቷል። ፈረንሳይ በጨዋታው ፍጹም ብልጫ ወስዳለች። የተደራጀ መከላከል እና የመልሶ ማጥቃት የአጨዋወት ስልት የተከተለችው ሞሮኮ ግልጽ የግብ እድሎችን መፍጠር ተስኗታል። የ27 ዓመቱ ኪሊያን ምባፔ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ስምንት በማድረስ ከአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ ጋር በጎል እኩል በመሆን ሶስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል ብልጫ ወስዶ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ይገኛል። በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ 20 ጎሎች ከመረብ ላይ በማሳረፍ በምንጊዜም ከፍተኛ አስቆጣሪነቱ ከሜሲ (21 ጎል) በአንድ አንሶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ምባፔ በዓለም ዋንጫው የጥሎ ማለፍ ምዕራፍ 12ኛ ጎሉን በማስቆጠር በውድድሩ አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል። ለብሔራዊ ቡድኑ 64ኛ ጎሉን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ምባፔ በ77ኛው ደቂቃ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ ወጥቷል። የባለንዶር ባለቤቱ ኡስማን ዴምቤሌ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አምስተኛ ጎሉን አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ፈረንሳይ ግማሽ ፍጻሜውን የተቀላቀለች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች። በዓለም ዋንጫው ለግማሽ ፍጻሜ ስታልፍ የአሁኑ ለሰባተኛ ጊዜ ነው። ፈረንሳይ በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ሞሮኮ የዓለም ዋንጫ ጉዟዋ ሩብ ፍጻሜው ላይ አብቅቷል። ለተከታታይ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የመግባት ህልሟ ሳይሳካ ቀርቷል። በሩብ ፍጻሜው ላይ አፍሪካን የወከለችው ብቸኛ ሀገር ሞሮኮ ከውድድሩ ተሰናብታለች። የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር ከተሳተፉ 10 ቡድኖች መካከል የተሻለ ርቀት መጓዝ ችላለች። ሞሮኮ በ22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ የአፍሪካ ሀገር መሆኗ የሚታወስ ነው። በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ አፍሪካ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ 10 ሀገራት አሳትፋለች።
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ዋንጫን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ አነሳ
Jul 9, 2026 313
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2 /2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 0 አሸንፏል። ረፋድ ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጋናዊው አጥቂ ኮንኮኒ ሃፊዝ በ47ኛው እና በየነ ባንጃ በ99ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጨዋታውን በርካታ ደጋፊዎች በስታዲየም በመገኘት ተከታትለውታል። ውጤቱን ተከትሎ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ዋንጫን አንስቷል። በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ46 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዞ ላጠናቀቀው ወልዋሎ የዛሬው ድል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ነው። የኢትዮጵያ ዋንጫ ድሉ በ1948 ዓ.ም ለተመሰረተው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ትልቅ ከሚባሉ ስኬቶች መካከል የሚጠቀስ ነው። ሲዳማ ቡና በአህጉራዊ ውድድር ተሳትፎውን በማረጋገጡ ምክንያት፣ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የውድድር ደንብ መሰረት ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን ተከትሎ የጨዋታውን ውጤት ሳይጠብቅ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት መሳተፉን ማረጋገጡ የሚታወስ ነው። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና ለተከታታይ ዓመት ለኢትዮጵያ ዋንጫ ቢደርስም ዋንጫውን ለመጀመሪያ ጊዜ የማሸነፍ ህልሙን ማሳከት አልቻለም። የዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ሲዳማ ቡና፣ ዓመቱን በሁለት ዋንጫ የማጠናቀቅ ፍላጎቱ ሳይሳካ ቀርቷል። ሲዳማ ቡና ፕሪሚየር ሊጉን ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ያነሳ ሲሆን ይህን ተከትሎም በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን አረጋግጧል። ሁለቱ ቡድኖች በቀጣዩ ዓመት ኢትዮጵያን በአህጉራዊ የክለብ ውድድሮች ላይ ወክለው ይሳተፋሉ። በ1937 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮጵያ ዋንጫ የ80 ዓመት ታሪክ ያለው አንጋፋ ውድድር ነው።
በክልሉ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናማና አምራች ዜጋን የማፍራት ሥራው ይጠናከራል
Jul 9, 2026 239
ሆሳዕና፤ ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦በማዕክላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ባህል በማድረግ ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራትና አብሮነትን ለማሳድግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠናከር የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሠራተኞችና ሃላፊዎች የተሳተፉበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርሀግብር ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል። የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ባህል በማድረግ ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራትና የአብሮነት እሴትን ለማጠናከር እየተሰራ ነው። በየአካባቢው የሚካሄደው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናማና አምራች ዜጋ ለማፍራት ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፣ የእርስ በርስ ግንኙነትን በማሳደግ በኩል ፋይዳው የጎላ በመሆኑም ስፖርቱን ለማስቀጠል ይሰራል ብለዋል። የዛሬው መርሀግብር ስፖርትን ባህል የማድረግ ሥራን ከማጠናከር ባለፈ ወጣቶች በበጎ ፍቃድ ሥራ እንዲሳተፉ ያለመ እንደሆነና መሰል መርሀግብሮችም በየአካባቢው እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የቢሮው ምክትል ሀላፊና የስፖርት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሰይፈ አለሙ በበኩላቸው እንደገለጹት በስፖርት ልማት ዘርፉ ክልሉ ያለውን አቅም ለይቶ መጠቀም የሚያስችል ሥራ እየተሰራ ነው። ለእዚህም ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራዎችን ለማስፋትና በሁሉም የስፖርት ዘርፍ ታዳጊና ተተኪ ስፖርተኞችን በማፍራት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አመልክተዋል። በተያዘው ክረምት ክልሉን የሚወክል የሰርከስ ቡድን ለማቋቋም መታቀዱን የገለጹት ሀላፊው የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችም ብቃት ያላቸው ወጣቶችን ለመለየት አይነተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ከተሳተፉት የማህበረሰብ ክፍሎች መካከል አቶ ብዙአየሁ ሀይሌ እና አቶ አብድልፈታ ናስር ጤናቸውን ለመጠበቅና የተሟላ ስብዕና ለመገንባት በአካል ብቃት እንቅስቃሴ በመርሀግብሩ ላይ መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ስፖርቱ በተለይ የእርስ በርስ ግንኙነታቸውን ከማጠናከር ባለፈ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን በጋራ ለማከናወን ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸውም ገልጸዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ ከተለያዩ መዋቅሮች የተውጣጡ ስፖርተኞችም መሳተፋቸው ታውቋል።
ፈረንሳይ ከሞሮኮ፦ ማን ወደ ግማሽ ፍፃሜው ያልፋል?
Jul 9, 2026 393
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ከእንድ ቀን እረፍት በኋላ ዛሬ በሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ይመለሳል። ምሽት አምስት ላይ ፈረንሳይ ከሞሮኮ በቦስተን ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ፈረንሳይ በ16ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ፓራጓይን በመርታት በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ ለ10ኛ ጊዜ ወደ ሩብ ፍጻሜው ገብታለች። ተጋጣሚዋ ሞሮኮ ከዓለም ዋንጫው አዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችውን ካናዳን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ሞሮኮ በዓለም ዋንጫው ታሪክ ሁለት ጊዜ ሩብ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች። ሁለቱ ቡድኖች ከዚህ ቀደም በዓለም ዋንጫው አንድ ጊዜ ተገናኝተዋል። ኳታር እ.አ.አ በ2022 ባዘጋጀችው 22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜው ተገናኝተው ፈረንሳይ 2 ለ 0 አሸንፋለች። ቴዎ ሄርናንዴዝ እና ራንዳል ኮሎ ሙዋኒ በወቅቱ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው። ሞሮኮ በጨዋታው ሽንፈት ቢገጥማትም በዓለም ዋንጫ ታሪክ ግማሽ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያ ሀገር በመሆን ታሪክ ሰርታለች። ሁለቱ ሀገራት በአጠቃላይ በውድድር እና በወዳጅነት ጨዋታዎች ላይ ስድስት ጊዜ ተገናኝተዋል። ፈረንሳይ አራት ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዛለች። ሞሮኮ አንድ ጊዜ ስታሸንፍ በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። ሞሮኮ በታሪኳ ፈረንሳይን ማሸነፍ የቻለችው አንድ ጊዜ ብቻ ሲሆን እሱም እ.ኤ.አ. በ1998 በንጉሥ ሀሰን ሁለተኛ ዋንጫ ላይ ሁለት እኩል ተለያይተው በፍጹም ቅጣት ምት 6 ለ 5 ያሸነፈችበት ጨዋታ ነበር። በነዚህ ስድስት ጨዋታዎች ላይ ፈረንሳይ 14 ጎሎችን ስታስቆጥር፣ ሞሮኮ 7 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። የዓለም ዋንጫውን ታነሳለች ተብላ ሰፊ ግምት ያገኘችው ፈረንሳይ የማጥቃት ኃይሏ ለተጋጣሚዎቿ የራስ ምታት ሆኗል። የ27 ዓመቱ ኪሊያን እምባፔ በዘንድሮው ውድድር 7 ግቦችን በማስቆጠር እና ሁለት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል ተመሳሳይ የግብ መጠን ያለውን አርጀንቲናዊውን ሊዮኔል ሜሲ በመብለጥ የኮከብ ግብ አግቢነቱን እየመራ ይገኛል። ምባፔ በዓለም ዋንጫው በአጠቃላይ 19 ግቦችን ከመረብ ላይ ያሳረፈ ሲሆን ከምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪው ሜሲ (20 ጎሎች) በአንድ ግብ ዝቅ ብሎ ይገኛል። ማይክል ኦሊሴ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አምስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል ድንቅ ብቃቱን እያሳየ ይገኛል። በሞሮኮ በኩል ሶስት ግቦችን በዓለም ዋንጫው ያስቆጠረው የ25 ዓመቱ አጥቂ ኢስማኤል ሳይባሪ ከካናዳ ጋር በነበረው ጨዋታ ባጋጠመው የጡንቻ መሳሳብ ጉዳት ከዛሬው ጨዋታ ውጪ ሆኗል። የሳይባሪን ቦታ ሶፊያን ራሂሚ በዛሬው ጨዋታ እንደሚሸፍን ይጠበቃል። በዓለም ዋንጫው በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን ያስቆጠሩት አዜዲን ኡናሂ እና ሶፊያን ራሂሚ የማጥቃት እንቅስቃሴውን በዋነኛነት ይመሩታል። ምርጥ ጓደኛማቾች እየተባሉ የሚጠሩት አሽራፍ ሀኪሚና ኪሊያን እምባፔ በጨዋታው ላይ የሚኖራቸው ፉክክር ተጠባቂ ሆኗል። ፈረንሳንይ ጨዋታውን የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት ብትወስድም ሞሮኮ ጠንካራ ተፋላሚነቷን ታሳያለች ተብሎ ይጠበቃል። የዛሬው ጨዋታ አሸናፊ በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ይገናኛል።
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን እያሳደገ ነው
Jul 9, 2026 473
ደብረ ብርሃን፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነዋሪዎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ የክረምቱን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በሲያደብርና ዋዩ ወረዳ "ጋራ መየ" ተፋሰስ ዛሬ አካሂዷል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደሰ ማሙሻ እንዳሉት ፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የለሙ ተፋሰሶች አርሶ አደሩ ከእለት ፍጆታው ያለፈ ምርት ለማምረት የሚያስችለውን አቅምን ፈጥሮለታል። በዋናነትም በመኖ ልማት፣ በእንስሳት እርባታና ማድለብ፣ በንብ ማነብ ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፎች እንዲሰማሩ ማስቻሉን ገልጸዋል። በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዞን ደረጃ በ36 ሺህ 284 ሄክታር መሬት ላይ ከ298 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ነው ያሉት። በዘንድሮው ዓመት የሚተከሉት ችግኞች የዞኑን የደን ሽፋን ከፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል። በክረምቱ ሁለት ነጥብ አራት ሚሊዮን የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በበኩላቸው ፤ህብረተሰቡ በየዓመቱ ችግኝ በመትከል ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጀመረውን ስራ አጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ሲሉ አሳስበዋል ። የሚተከሉ ችግኞችም አሁን ያለውን አርሶ አደርና ወጣት ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር የመጪውን ትዉልድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የሲያ ደብርና ዋዩ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ደሱ ምክረ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሚተከሉ ችግኞች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸዉና ለአካባቢ ስነ ምህዳር ጥበቃ ከፍተኛ ፋይዳ የሚያበረክቱ ናቸው። በወረዳው በያዝነው ክረምት ስምንት ነጥብ አራት ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የሚያስችል የቦታ ዝግጅት ተካሂዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል። የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ዓለማየሁ ያዴቴ እንደገለጹት፤በዘንድሮው ዓመት ከዚህ በፊት ከተከሏቸው ችግኞች 30 ሺህ ብር ገቢ ማግኘታቸውን ጠቁመዋል ። የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የጽድቀት ምጣኔያቸውን ለማሳደግ እንሰራለን ሲሉም ገልጸዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይም ከዞንና ከወረዳ የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን በክረምቱ ወቅት በሁለት ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ልማት ይካሔዳል
Jul 9, 2026 247
ደብረ ማረቆስ ፤ሃምሌ 2/2018(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁለት ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍን የፍራፍሬ ልማት እንደሚካሔድ የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ። በመምሪያው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባለሙያ አቶ ተሾመ በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤በተያዘው ክረምት ለሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአንድ ሚሊዮን በላይ የፍራፍሬ ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል። ለተከላ ከተዘጋጁት ችግኞች ውስጥ የአቮካዶ፣ ብርቱካን ፣ ማንጎ ፣ ሎሚ ፣ ፓፓያ እና የአፕል ዝርያዎች እንደሚገኙበት ነው ያመለከቱት። የችግኝ ተከላው በሁለት ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የሚካሔድ ሲሆን እስካሁን በተደረገው ጥረት ከ80 ሺህ በላይ የፍራፍሬ ችግኝ መተከሉን ገልፀዋል ። በዚሁ የፍራፍሬ ችግኝ ተከላ ከ20 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን እንደሚሳተፉም ነው ያመለከቱት። በአሁኑ ወቅትም አርሶ አደሩ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በፍራፍሬ ልማት ተሳትፎ ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥ የተሻሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ለአብነትም ባለፉት ጥቂት ዓመታት ቡናን ጨምሮ ሌሎች የፍራፍሬ አይነቶችን በማልማት አርሶ አደሩ ቋሚ ገቢ በማግኘት ጥሪት እንዲያፈራ እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በየደረጃው ያለው የዘርፉ አመራርና በላሙያም አርሶ አደሩን በመደገፍ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት ጥቂት ዓመት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በፍራፍሬ ልማት መሸፈኑን ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በአቮካዶ ምርት የተመዘገበውን ስኬት በቆላ ፍራፍሬ ልማት ለመድገም እየተሰራ ነው
Jul 8, 2026 503
ገንዳ ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- የአቮካዶ ምርትን ወደ ውጭ በመላክ እየተመዘገበ ያለውን ስኬት በሌሎች የቆላ የፍራፍሬ ልማቶች ለመድገም የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በምዕራብ ጎንደር ዞን "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዞኑ በገንዳውኃ ጊዮርጊስ ተፋሰስ ተጀምሯል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊና ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንደገለጹት ፤ለዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ ችግኞች በማዘጋጀት የተከላ ስራ ተጀምሯል። ለተከላ የተዘጋጁት ችግኞችም ለምግብነት የሚውሉ፣ ቀጥተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የደን ዝርያዎችና ለእንስሳት መኖ የሚውሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዞኑ ለቆላ ፍራፍሬ ልማት ያለውን ምቹ የአየር ንብረት፣ ለም መሬትና ከፍተኛ የውሃ አማራጭ በመጠቀም የተሻለ ውጤት ለማምጣት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። "ለፍራፍሬ ልማት ቀደም ብለን ተዘጋጅተናል" ያሉት ኃላፊው ከ200 ሺህ በላይ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች በክላስተር መዘጋጀቱን ጠቁመው ከ600 ሺህ በላይ የሙዝ፣ ማንጎ ፣ ዘይቱን ፓፓያና ብርቱካን ችግኞች ይተከላሉ ብለዋል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በበኩላቸው “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የዞኑ ሕዝብ በንቃት በመሳተፍ ተጠቃሚነቱን እንዲያሳድግ አሳስበዋል። ችግኞችን ከመትከል ባለፈ፣ በዘላቂነት ፀድቀው ለታለመላቸው ፍሬ እንዲበቁ ተገቢውን እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባም ነው ያመለከቱት። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት ወጣት አሸናፊ ታፈረና ደጉ ገብረ እግዚአብሔር በበኩላቸው፣በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች በአጭር ጊዜ ለውጥ ማምጣታቸውን እንደተመለከቱ ተናግረዋል። እየተገኘ ያለውን ጥቅም ለማሳደግም በክረምቱ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ያለምንም ቀስቃሽ በፈቃዳቸው በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን አስረድተዋል። በማስጀመሪያው መርሐግብሩ ላይ የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች፣ የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የአረንጓዴ አሻራ እያስገኘ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል
Jul 7, 2026 644
ጎንደር፤ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ):- የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር እያስገኝ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማስቀጠል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኜው ገለጹ። ከተማ አስተዳደሩ የክረምት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዘዞ ክፍለ ከተማ በአባ ሳሙኤል ፓርክ ዛሬ አስጀምሯል። ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ቻላቸው ዳኜው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር ባጭር ጊዜ ውስጥ ዘርፈ ብዙ እና ተጨባጭ ለውጥ ለማስመዝገብ ያስቻለ ነው። በመርሃ- ግብሩ የለሙ ተፋሰሶች አርሶ አደሩ በመስኖ፣ በእንስሳት እርባታና ማድለብ፣ በንብ ማነብ ፣ በመኖና ሌሎች የልማት ዘርፎች በመሳተፍ ተጠቃሚ መሆን የቻለበት ነው ሲሉ ገልፀዋል። በተለይም በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት አርሶ አደሩ ዘላቂና ተጨማሪ ሃብት እንዲያፈራ መርሃ ግብሩ ሰፊ እድል ለመፍጠር እያስቻለ መሆኑንም ነው ያነሱት። በመሆኑም በዘንድሮው ዓመትም የአትክልት ፍራፍሬና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ላይ በማተኮር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እንደሚካሔድ አስረድተዋል። የከተማ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አበራ አደባ ፤በበኩላቸው በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ476 ነጥብ 5 ሔክታር መሬት ላይ 4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞች እንደሚተከሉ ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በተካሄደው መርሃ ግብርም 758 ሺህ ዜጎችን በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። በዘንድሮ ዓመትም ባለፉት ዓመታት የተገኘውን ተጠቃሚነት ለማስፋትም 500 ሺህ የአቡካዶ፣ ሙዝ፣ ማንጎና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን አስገንዝበዋል። የተተከሉ ችግኞችን የመጽደቅ ምጣኔ 95 በመቶ ለማድረስ ማህበረሰቡን ያሳተፈ የእንክብካቤና ጥበቃ ስራ እንደሚከናወን አስገንዝበዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለእንስሳት መኖ፣ ለንብ ማነብ፣ ለከብት ማድለብና በወተት ልማት ዘርፍ እድገት ማስመዝገብን ጨምሮ ስርአተ ምግብም እንዲሻሻል ማድረጉን አስረድተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 17586
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 11575
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 10372
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 10270
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
ላሊበላ፦ ከዓለም አቀፍ ቅርስነት እስከ ባህል ዲፕሎማሲ ማዕከልነት
Jul 9, 2026 276
በሙሴ መለሰ ከ40 በላይ ኤምባሲዎችን ጨምሮ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የተወከሉ ከ70 በላይ ከፍተኛ ዲፕሎማቶችና የልማት አጋሮች ከአፍሪካ እጅግ አስደናቂ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶች መገኛ በሆነችው በታሪካዊቷ የላሊበላ ከተማ ከሰሞኑ ጉብኝት አድርገዋል። ይህ ታሪካዊ ጉብኝት በዓለም አቀፍ ደረጃ የላሊበላን ውቅር አብያተ ክርስቲያናት የመንከባከብና የመጠበቅ የጋራ ቃልኪዳንን በድጋሚ ለማደስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ይህን ዲፕሎማሲያዊ ጉብኝት ያዘጋጀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ከቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን፣ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ ከአማራ ክልል መንግሥት፣ ከላሊበላ ከተማ አስተዳደር እና በፈረንሳይ መንግሥት ድጋፍ ከሚንቀሳቀሰው “ዘላቂ ላሊበላ” ፕሮጀክት (Sustainable Lalibela Project) ጋር በመሆን ነው። ላሊበላ እ.አ.አ በ1978 በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ መዝገብ ላይ የሰፈሩት ድንቅ አብያተ ክርስቲያናትን ይዛለች። ከስምንት መቶ ዓመታት በፊት (በ13ኛው ክፍለ ዘመን) ከአንድ ወጥ አለት ተፈልፍለው የታነጹት 11ዱ ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናት፤ ዛሬም ድረስ መላውን ዓለም በአድናቆት የሚጎበኛቸው፣ የጥንታዊ ምህንድስና እና የመንፈሳዊነት ጥልቅ መገለጫዎች መሆናቸውን ዩኔስኮ ጉብኝቱን አስመልክቶ ባወጣው ጽሁፍ ላይ አመልክቷል። በጉብኝቱ የተሳተፉት ዲፕሎማቶች እንደ ቤተ መድኃኔዓለም፣ ቤተ ማርያም፣ ቤተ ጊዮርጊስ፣ ቤተ አማኑኤል እና ቤተ ቅዱስ መርቆሬዎስ ያሉትን አብያተ ክርስትያናት ተመልክተዋል። ዲፕሎማቶቹ ላሊበላን “ከዚህ ዓለም ስሪት የላቀ እፁብ ድንቅ ጥበብ” ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ቅርሶቹ የጥንታውያኑን አባቶች ድንቅ የምህንድስና ጥበብና የስነ-ህንጻ ልህቀት ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ መሆናቸውን በአድናቆት ተናግረዋል። ዲፕሎማቶቹ ከአብያተ ክርስቲያናቱ ጉብኝት ባሻገር ከነዋሪው፣ ከአካባቢው ማህበረሰብ እና ከሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት አድርገዋል። ይህ ውይይት ልዑካኑ የላሊበላን ህያው ቅርስ ለመጠበቅ የሚደረጉ ጥረቶችን እና ይህንን ታሪካዊ ስፍራ ለቀጣዩ ትውልድ ለማቆየት እየገጠሙ ያሉ ወቅታዊ ተግዳሮቶችን መፍታት ስለሚቻልበት ሁኔታ በተሻለ መልኩ ለመረዳት አስችሏቸዋል። ጉብኝቱ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በቅርቡ በአካባቢው ከተከሰቱ ፈተናዎች በኋላ፣ የላሊበላን የቱሪዝም እንቅስቃሴ መልሶ ለማገገም እና ለማነቃቃት ትልቅ ዕድል ፈጥሯል። ጎብኚዎቹ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ባህል ሰዎችን በማቀራረብና የእርስ በርስ መግባባትን በማጠናከር ረገድ ስላለው የማይተካ ሚና አጽንኦት ሰጥተዋል። ዩኔስኮ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎ እና ከሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ለፈረንሳይ መንግሥት እና ለጉብኝቱ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናውን አቅርቧል። ጉብኝቱ የላሊበላን ባህላዊ፣ መንፈሳዊና ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶች እና እሴቶች ባሉበት ለተተኪው ትውልድ ለማሻገር ያለውን ዓለም አቀፍ ቁርጠኝነት ያረጋገጠ መሆኑን ድርጅቱ አመልክቷል። ዩኔስኮ በቅርሱ አያያዝ፣ ጥበቃ እና ቀጣይነት ላለው አስተዳደር ዙሪያ ከኢትዮጵያ መንግስት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ቴክኒካዊ ትብብር እና በአቅም ግንባታ ለበርካታ አስርት አመታት በቅርበት ሲሰራ መቆየቱንና የቅርሱን ዓለም አቀፍ ሀብትነት ጠብቆ ለማቆየት ይህንኑ ተግባሩ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በጽሁፉ አረጋግጧል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jul 5, 2026 1382
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018(ኢዜአ):- የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? ኢትዮጵያ እያከናወነች ነው የገጠር ትራንስፎርሜሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት የተጀመረው የከተሞች ኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩም ተስፋፍቶ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗርና አመጋገብ እንዲሁም ጤናን መሰረት በማድረግ የገጠር ኮሪደር ልማት በመከናወን ላይ ይገኛል። ለጤናም ይሁን ለኑሮ ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ለዘመናት በተመሳሳይ ሁኔታ የኖረው አርሶና አርብቶ አደሩ አሁን ላይ መሰረታዊ የአኗኗር ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በገጠር የኮሪደር ልማት የሰዎችና እንስሳት መኖሪያ እየተለየ፤ በባዮ ጋዝ እና በፀሃይ ብርሃን በሚሰራ የሃይል ምንጭ መብራት ማግኘትና ምግብ መስራት የተቻለበት፤ በጓሮ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎችን መመገብ የሚቻልበት ዘመናዊ አኗኗር ጀምረዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን የልማት እንቅስቃሴው በጅምር ላይ ቢሆንም በብዙ አካባቢዎች እየተስፋፋ ሞደል መንደሮች እየተበራከቱ መጥተዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ሀማሳ በ79 ነጥብ 4 ሄክታር መሬት ላይ የተሰራው ሞዴል መንደር የዚሁ ጥረት ማሳያ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቆ ለነዋሪዎች የተላለፈው የሀማሳ ሞዴል መንደር በአንድ ግቢ ውስጥ የንጽህና መጠበቂያ፣ የተደራጀ የቤት እንስሳት ማቆያ፣ በባዮ ጋዝ የሚሰራ የሃይል አቅርቦትን እንዲሁም የተሟላ የጓሮ ግብርናን ማእከል አድርጎ የተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም መንግሥት በተለያዩ የገጠር አካባቢዎች ሞዴል ቤቶችን መስራቱን አስታውሰው ከዚህ በመነሳት ነዋሪዎቹ በራሳቸው ተነሳሽነት የራሳቸውን መኖሪያዎች መገንባት ጀምረዋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው ''ንጽህና ካለ ጤና አለ፤ ምግብ ካለ ጤና አለ፤ የተስተካከለ ኮሪደር ካለ ሰላም አለ። እነዚህ ጉዳዮች ከፍተኛ ግምት ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል። የዜጎቻችንን ሕይወት ይቀይራሉ፤ የአኗኗር ዘዬአችንን ያሻሽላሉ፤ ኢትዮጵያን ወደ ምናስበው ከፍታ ወደ ምናስበው መሻሻል የመውሰድ አቅም አላቸው'' ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ቀጥሎ በጋሞ ዞን የ'ዮ ሆልዲንግ’ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከጥቂት ዓመታት በፊት ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚሆን የድንጋይ ከሰል ከውጭ ሀገር ለማስገባት እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር ውጪ የሚደረግ መሆኑን አንስተዋል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ የተለያዩ የከሰል ማምረቻ ፋብሪካዎች ተመርቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውንና ይህም የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ ለውጭ ገበያ የማቅረብ እድል ይፈጥራል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአርባምንጭ ዘመናዊ የኮንፈረንስ ሪዞርት መርቀው ስራ ያስጀመሩ ሲሆን በዶርዜ ሎጅ እና አካባቢው መሰረተ ልማቶችን እንዲሁም የአርባ ምንጭ ከተማን የኮሪደር ልማት፤ በከተማዋ የሚገኘውን ኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓንም ጎብኝተዋል። በሁሉም ዘርፎች ኢትዮጵያ ማከናወኗን አጠናክራ ቀጥላለች፤ እድገትና ማንሰራራቷ ላይቀለበስ ጉዞውን ቀጥሏል። ከዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች አንዱ የቱሪዝም ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት እንዳስታወቀው የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በዓለማችን ከፍተኛ ተጓዦች ከተመረጡ የዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች መካከል አንዱ ሆኗል። በዩሮኒውስ የዜና አውታር በተደረገ ጥናት፤ ሁሉንም የዓለም ክፍሎች ያዩ አንጋፋ ተጓዦች ካስቀመጧቸው ተወዳጅ የዩኔስኮ የዓለም ቅርሶች መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በግንባር ቀደምትነት ተቀምጧል። በዚሁ ሳምንትም ከአርባ በላይ ሀገራት እና ከአሥር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ዲፕሎማቶች የላሊበላ ከተማና ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። ይህ ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑክ በቆይታው ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን፣ የሕንጻ ጥበብ እና የኢንጂነሪንግ ጥበብ ማስተርፒስ እንዲሁም የሃይማኖትና የታሪክ ሕያው ምስክር የሆኑትን የዓለም ቅርስ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አስተማማኝ መከታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ያሰለጠናቸውን ተመራቂዎች በዚሁ ሳምንት አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ሰራዊቱ የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝ መልኩ እየጠበቀ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ ታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች ግንባር ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያን ከባሕር ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ “ፅምዶ” በሚል የተሰለፉ አካላት ስለመኖራቸው ተናግረዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአደረጃጀት ልዩ እና በዘመናዊ ትጥቅ ተጠናክሮ በማንኛውም ሁኔታ ለሀገሩ ክብርና ሉአላዊነት መጠበቅ አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል። የ12ኛ ክፍል ፈተና በሳምንቱ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ስኬታማ በሆነ መልኩ ተከናውኗል። በሁሉም አካባቢዎች ተፈታኞች በበይነመረብ (ኦንላይን) እንዲሁም በወረቀት እንደየ ዝግጅቱና ምቹ ሁኔታውን መሰረት በማድረግ ፈተናውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በገጠር ኮሪደር አዲስ የህይወት ምእራፍ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የጊምቦ ወረዳ በተገነባው ሞዴል የገጠር መንደር የሚኖሩ አርሶ አደሮች አዲስ የህይወት ምእራፍ መጀመራቸውን ገልጸዋል። የኤሌክትሪክና ሌሎች አገልግሎቶች የተሟላለት የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር የአኗኗር ዘይቤያችንን ምቹና ዘመናዊ አድርጎታል ያሉት ነዋሪዎቹ ይህንን ላደረጉ ሁሉ እናመሰግናለን ብለዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ የተገነባውን የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የግብርናና ገጠር ሽግግርን እውን በማድረግ የአርሶ አደሩን አኗኗር ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ገልፀው የመብራት፣ የውሃ፣ የመንገድን ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን አርሶ አደሩ በአቅራቢያው ማግኘት የሚያስችልና የኢኮኖሚ አቅሙን የሚያሳድጉ መሆናቸውን በወቅቱ ተናግረዋል። በቀጣይም ተግባሩን በማስፋት ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግን ፍልሰት ለማስቀረት በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ አኔ ዲማ ወረዳ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰኣዳ አብዱረህማንና የከተማው ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎችም የአከባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰዓዳ አብዱረህማን በወቅቱ፤ ዛሬ የምንተክላቸው ችግኞች ለሀገራችን ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ የሚሰጡ ናቸው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለትውልድ ቀጣይነት አስተማማኝ ዋስትና ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)፤ በሸገር ከተማ የአካባቢውን አረንጓዴነት ለማረጋገጥና ኢኮኖሚውን ለመደገፍ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን የተለያዩ ዝርያ ያላቸውና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር ገብተናልም ብለዋል። የባቡር መስመር ጥገና የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በቅርቡ የጥገና ስራው የተጀመረውን የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ የባቡር መስመር ፕሮጀክት የጥገና ሂደት በዚሁ ሳምንት ጎብኝተዋል። ከአዋሽ -ኮምቦልቻ -ሃራ ገበያ 392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን ፕሮጀክት በአራት አቅጣጫ የጥገና ሥራው እየተከናወነ መሆኑም ታውቋል። ለልማት ተነሽዎች የተገነቡ ቤቶች በዚሁ ሳምንት የጅማ ከተማ አስተዳደር ለልማት ተነሺዎች ያስገነባውን 300 መኖሪያ ቤቶች መርቆ ማስረከቡን እንመለከታለን። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ፤ በክልሉ በገጠርም ይሁን በከተሞች ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሃ ቀመር፤ በከተማው በርካታ ፕሮጀክቶች በመንግስት እየተከናወኑ እንደሆኑና የተጠናቀቁትም ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በከተማዋ በዚህ አመት 80 የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ጠቅሰው ዛሬ ለልማት ተነሺዎች ተገንብተው የተላለፉ መኖሪያ ቤቶች የዚሁ ጥረት አንድ አካል ናቸው ብለዋል። እነዚህ መኖሪያ ቤቶች ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው ግንባታቸው ተጠናቆ ለ300 አባወራና እማወራዎች ተላልፈዋል ብለዋል።
ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች
Jun 29, 2026 3889
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • ምንድንነት የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም ‘አስም’ እንደሚባልም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የኪንታሮት ህመም እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? • ምልክቶች የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ጠቁመዋል። ምልክቶቹም በአብዛኛው በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ አስገንዝበዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር)፣ የእንስሳት አይነ ምድር ሽታዎች ለዚህኛው አስም አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን አስረድተዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑንም ተናግረዋል። • አጋላጭ (ለህመሙ መባባስ) መንስዔዎች አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የዓየር ብክለት፣ ጭስ)፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ዓይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? 👉ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎችዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ 👉 በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ 👉 በቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ ሙቀት የሚሰጡ መከላከያ ልብሶችን መልበስ፤ 👉 ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ • ሕክምናው የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የዓየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ከ 3 እስከ 10 በመቶ ያህሉ የዓለም ሕዝብ በአስም ተጠቂ መሆኑንም ጠቁመዋል። #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢዜአ #የጤና_ነገር
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 3618
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ትንታኔዎች
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 2091
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 2135
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 2184
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 5908
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 8328
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 19560
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 12617
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 18367
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 4536
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 3334
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።