ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የአምቦ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መሻሻል ከእንግልት ታድጎናል - ተገልጋዮች
Apr 30, 2026 5
አምቦ፤ ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡- የአምቦ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መሻሻል ከእንግልትና አላስፈላጊ ወጪ ታድጎናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ።   ሻምበል አንዷለም ገረመው በሰጡት አስተያየት፤ በማዘጋጃ ቤቱ አንድ ጉዳይ ለማስፈጸም የቀናት ምልልስን በመጠየቁ ሳቢያ የጊዜ ብክነት ያጋጥም ነበር ብለዋል። አሁን አገልግሎቱ የዘረጋው ፈጣን አሠራር ተደራጅተው መሬት ለመጠየቅ የመጡበትን ጉዳይ በፍጥነት ለማስፈጸም እንዳገዛቸው ተናግረዋል። የማዘጋጃ ቤቱ ቀልጣፋና ዘመናዊ ሂደትን የተከተለ አሠራር እንግልትን የቀረፈ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል፡፡ በማዘጋጃ ቤቱ የተጀመረው ዘመናዊ አገልግሎት የመጡበትን ካርታ የማውጣት ጉዳይ በአጭር ጊዜ እንዲያጠናቅቁ እንዳስቻላቸው የገለጹት ደግሞ ወርቅነሽ ዴሬሳ ናቸው።   ያዴሳ ቡልቱማ በበኩላቸው በነባሩ አሠራር መረጃ ጠፋ በሚል ባለ ጉዳይን የማጉላላት ሁኔታ እንደ ነበር አውስተው፤ አሁን አገልግሎት አሰጣጡ በመሻሻሉ ጉዳያቸውን በፍጥነት ማስፈጸማቸውን አስረድተዋል።   ማዘጋጃ ቤቱ የአገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ባለ ጉዳዮች በፍጥነት የሚስተናገዱበትን ሂደት ለማሳካት የሰው ኃይልና በግብዓት የማሟላት ሥራ መሠራቱን ያስታወቁት ደግሞ የአምቦ ከተማ አሥተዳደር ማዘጋጃ ቤት ምክትል ኃላፊ ሙሊሳ ፈዬራ ናቸው። ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በማስደገፍና መልሶ በማደራጀት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይ ለማስፈጸም ይወስድ የነበረን ምልልስ በማስቀረት ተገልጋዮች ባጠረ ጊዜ ጉዳያቸውን እንዲያጠናቅቁ መደረጉን አውስተዋል።
የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ አስቻይ ምኅዳር ፈጥሯል-አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ
Apr 30, 2026 64
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ንግድና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ለዓለም አቀፍ አልሚ ባለሃብቶች ምች ምኅዳርን ፈጥሯል። የዓለም አቀፍ አልሚ ባለሃብቶችም የኢትዮጵያን ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ በመጠቀም በተለያዩ የልማት መስኮች እንዲሰማሩ እያደረገ ይገኛል። ‎የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ 3 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት መሳብ ችላለች። በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ዕድገትና ብልፅግናን የሚያፋጥን ሰፊ የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድል ያላት ሀገር ናት። የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንትን አማራጭ ለማስፋት መንግስት የሚወስዳቸው የፖሊሲ አማራጮችም የሚደነቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢኮኖሚ ዘርፍ ልማትን ለማበረታታት የተወሰዱ የፖሊሲ ማሻሻያ ተግባራትም ኢትዮጵያን አፍሪካዊት ተመራጭ የንግድና ኢንቨስትመንት መዳረሻ ሀገር እያደረጋት መሆኑን ተናግረዋል። በኢትጵያና ፈረንሳይ መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት የበለጠ ለማስፋትም በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኝ አንስተዋል። ፈረንሳይም የሀገራቱን ትብብር የበለጠ ማጠናከር የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎችን በመደገፍ ወደ ተሻለ የዕድገት ምዕራፍ ለማሸጋገር ድጋፍ እያደረገች መሆኗን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የፈረንሳይ አልሚ ባለሃብቶች በተለያዩ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አማራጮቻቸውን እያስፋፉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን ሰፊ የንግድና ኢንቨስትመንት አማራጮቻቸውን የበለጠ እንዲያሰፉ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም የሁለቱን ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር የበለጠ በማጎልበት የጋራ ተጠቃሚነትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ዘንድሮ በሰሜን ሸዋ ዞን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ከ36 ሺህ ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ ችግኝ ይተከላል
Apr 30, 2026 43
ደብረ ብርሃን፤ ሚያዝያ 22/ 2018 (ኢዜአ)፡- በመጪው ክረምት በሚካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ከ36 ሺህ ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ ችግኝ እንደሚተከል የሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ አስታውቋል። ለመጪው ክረምት አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሚተከሉ 294 ሚሊየን ችግኞች እስካሁን መዘጋጀታቸውን በመምሪያው የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ቡድን መሪ ጌታነህ ተ/ማርያም ገልጸዋል።   በቀሪ ወራትም ፈጥነው የሚደርሱ ችግኞች ላይ በማተኮር የማዘጋጀት ሥራው እንደሚቀጥል ጠቁመዋል። በአጠቃላይም በመጪው ክረምት ከ36 ሺህ 260 ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ ችግኞች እንደሚተከሉ ለኢዜአ ተናግረዋል። ከአሁን በፊት የተተከሉ ችግኞች አርሶ አደሩን በእንስሳት ዕርባታና ማድለብ፣ በንብ ማነብ፣ በመኖ አቅርቦትና በሌሎች የሥራ ዘርፎች በማሰማራት ጥምር ግብርናን ለማስፋፋት ምቹ ሁኔታ ፈጥረዋል ብለዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት የለሙ 1 ሺህ 163 ተፋሰሶች የአፈር ለምነትን በማሻሻል፣ የገጸና ከርሰ ምድር ውኃን በማበልጸግና ለመስኖ ልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደጋቸውንም አክለዋል።
የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች መጠናከር አለባቸው
Apr 30, 2026 52
ጂንካ፤ ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ በንቅናቄ የተጀመረው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን አስገነዘቡ።   ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ የባሕር በር የማግኘት መብት እንዳላት በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ምስክር ከተማ ለኢዜአ አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ በአደባባይ እየተነሳ ያለው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ፤ የሀገርን ብሔራዊ ደኅንነት ከማስጠበቅ ባለፈ በቀጣናው ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማስፈን ያስችላል ብለዋል። ኢትዮጵያ ያለሕግ አግባብ በፖለቲካ ሴራ የተነጠቀችውን ወደብ መልሳ እንድታገኝ የተጀመረው በመርኅ ላይ የተመሠረተ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት መጠናከር እንዳለበት መክረዋል።   የባሕር በር አለመኖር ከሀገር ደኅንነትና ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር ስለሚያያዝ አጀንዳ ሊሆን ይገባል ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ጌታቸው ብርሃኑ ናቸው። ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የኢትዮጵያን እውነታ ከማሳወቅ ባለፈ ምሁራንን ያሳተፈ ጥምረት ፈጥሮ ሳይንሳዊ መረጃና ማስረጃዎችን መሠረት ያደረገ ሐሳብ የሚንሸራሸርበት መድረክ መፍጠር እንደሚገባም ጠቁመዋል። አጀንዳው ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የዘርፉ ምሁራንም ኅብረታቸውን በማጠናከር የሕብረተሰቡን ንቃተ-ኅሊና ማሳደግና የኢትዮጵያን እውነታ ለዓለም የሚያስገነዝቡ ሥራዎችን መሥራት አለበን ብለዋል።
የሚታይ
የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ አስቻይ ምኅዳር ፈጥሯል-አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ
Apr 30, 2026 64
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ንግድና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ለዓለም አቀፍ አልሚ ባለሃብቶች ምች ምኅዳርን ፈጥሯል። የዓለም አቀፍ አልሚ ባለሃብቶችም የኢትዮጵያን ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ በመጠቀም በተለያዩ የልማት መስኮች እንዲሰማሩ እያደረገ ይገኛል። ‎የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ 3 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት መሳብ ችላለች። በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ዕድገትና ብልፅግናን የሚያፋጥን ሰፊ የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድል ያላት ሀገር ናት። የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንትን አማራጭ ለማስፋት መንግስት የሚወስዳቸው የፖሊሲ አማራጮችም የሚደነቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢኮኖሚ ዘርፍ ልማትን ለማበረታታት የተወሰዱ የፖሊሲ ማሻሻያ ተግባራትም ኢትዮጵያን አፍሪካዊት ተመራጭ የንግድና ኢንቨስትመንት መዳረሻ ሀገር እያደረጋት መሆኑን ተናግረዋል። በኢትጵያና ፈረንሳይ መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት የበለጠ ለማስፋትም በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኝ አንስተዋል። ፈረንሳይም የሀገራቱን ትብብር የበለጠ ማጠናከር የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎችን በመደገፍ ወደ ተሻለ የዕድገት ምዕራፍ ለማሸጋገር ድጋፍ እያደረገች መሆኗን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የፈረንሳይ አልሚ ባለሃብቶች በተለያዩ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አማራጮቻቸውን እያስፋፉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን ሰፊ የንግድና ኢንቨስትመንት አማራጮቻቸውን የበለጠ እንዲያሰፉ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም የሁለቱን ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር የበለጠ በማጎልበት የጋራ ተጠቃሚነትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የቻይና ባለሃብቶችን የንግድና ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እያሳደገ ነው
Apr 29, 2026 668
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የቻይና ባለሃብቶችን የንግድና ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እያሳደገ መሆኑን በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ። አምባሳደር ቼን ሃይ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ እና ቻይና ታሪካዊና ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው። የኢትዮ-ቻይና ታሪካዊ ግንኙነት የልማት ትብብርን በማጎልበት የሀገራቱን ሁለንተናዊ ግንኙነት እያጠናከረ እንደሚገኝም ገልጸዋል። የሀገራቱ የሁለትዮሽ የንግድና ኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ አጋርነት ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ የጋራ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። የቻይና ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የሚሰማሩባቸው አዳዲስ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎችም ከፍተኛ ዕድገት እያስመዘገቡ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም የቻይና አልሚ ባለሃብቶችን የኢንቨስትመንት በራስ መተማመን በማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የፈጠረው የኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢም አዳዲስ ዕድሎችን መጠቀም የሚሹ በርካታ የቻይና ባለሀብቶችን እየሳበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የኢትዮ-ቻይና የኢኮኖሚ ትብብርም በግብርና፣ ኢንዱስትሪና የሰው ሃብት ልማት ሶስት ወሳኝ ምሰሶዎችን ማዕከል በማድረግ በስፋት እየተሰራበት መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ፈጣን የልማትና የዕድገት አቅጣጫ የሀገራቱን ስትራቴጂክ አጋርነት በማጠናከር ከፍተኛ አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል። የቻይና ባለሃብቶች የኢትዮጵያ የንግድና የአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ተሳትፎም የኢኮኖሚ ልማትና ሽግግርን በማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ተናግረዋል። የሀገራቱ በሰው ሃብት ልማት ትብብር የአዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በክህሎት የበለፀጉ ዜጎችን በማፍራት ወሳኝ ሚና እየተወጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በሚቀጥሉት ዓመታትም የሀገራቱን የንግድና ኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ አጋርነት የበለጠ በማጠናከር የሁለትዮሽ ግንኙነትን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራ ጠቅሰዋል።
በክልሉ ኢንተርፕራይዞችን ወደ ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር የተከናወኑ ተግባራት ውጤት አስገኝተዋል
Apr 29, 2026 414
ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንተርፕራይዞችን በመደገፍና በማብቃት ወደ ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ውጤት ማስገኘታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ የክልሉ ስራ እድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ "የኢንተርፕራይዞች ሽግግር ለእመርታዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው አውደ ርዕይና ባዛር እንዲሁም የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ደረጃ ሽግግር እውቅና መርሃ ግብር በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡   ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ኢንተርፕራይዞችን በማብቃት ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ውጤት አስገኝተዋል። ኢንተርፕራይዞቹ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።   በክልሉ ተወዳዳሪ ኢንተርፕራይዞችን ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የክልሉ ስራ እድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሙስጠፋ ኢሳ ናቸው።   በገጠርና በከተማ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ ከ25 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ መስኮች መሰማራታቸውን ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በጥቃቅንና አነስተኛ ደረጃ የሚገኙ 4ሺህ 948 ኢንተርፕራይዞችን የማሸጋገርና 495 ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን የመለየት ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል በሆሳዕና ከተማ የሚገኘው የጡማ ፕላስቲክ ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅ ሰለሞን ታሪኩ እና የእንጨትና የብረታብረት ማምረቻ ኢንተርፕራይዝ ሰብሳቢ ወጣት ዘርፍነሽ ሽብሩ የደረጃ ሽግግሩ ድርጅቶቻቸው ስራቸውን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲከውኑ ማስቻሉን ጠቁመዋል። ፋብሪካው ከ120 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገቡንና ከ150 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፍጠሩን አቶ ሰለሞን ተናግረዋል። ወጣት ዘርፍነሽ በበኩሏ ኢንተርፕራይዙ 10 ሚሊየን ብር ካፒታል ማስመዝገቡን ገልጻ 30 ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሯል ብላለች።
ኢትዮጵያ የአቪዬሽን መሰረተ ልማት በማሟላት የአፍሪካ አቪዬሽን መግቢያ በር መሆን የሚያስችላት ቁመና ላይ ናት
Apr 29, 2026 365
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአቪዬሽን መሰረተ ልማት በማሟላት የአፍሪካ አቪዬሽን መግቢያ በር መሆን የሚያስችላት ቁመና ላይ ናት ሲሉ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን ገለጹ። ዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ በአፍሪካ አቪዬሽን ዘርፍ ባሉ ችግሮች እና መፍትሔዎች ላይ ምክክር ይደረጋል። የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን እንደገለጹት፤ አፍሪካ አንድ ነጥብ አራት ቢሊየን የህዝብ ቁጥር ያላት ቢሆንም አህጉሪቱ በበቂ መጠን በአየር ትራንስፖርት ተሳስራለች ማለት አይቻልም።   ለዚህም የዋጋ መጨመር፣ የመሰረተ ልማት በበቂ ደረጃ አለመሟላት እና ወጥ የሆነ የአሰራር ስርዓት አለመኖር ዋነኞቹ ምክንያቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እንደ ሀገር በአቪዬሽን መሰረተ ልማት ላይ በሰፊው ኢንቨስት በማድረግ ላይ መሆኗን በመጠቆም፤ በቢሾፍቱ ግንባታው የተጀመረው ዓለምአቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክትም ተጠቃሽ መሆኑን ገልጸዋል። ግንባታው ሲጠናቀቅም የኢትዮጵያን አቅም ከማሳደጉ ባሻገር አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፍ መሰረተ ልማት ላይ የምታከናውነው ሥራ ሀገሪቷን የአፍሪካ አቪዬሽን መግቢያ በር (ጌት ዌይ) የሚያደርጋት መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በጠንካራ ሪፎርም ውስጥ እንዲያልፍ መደረጉን ጠቁመው፤ ይህም በኢትዮጵያ ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የበረራ አገልግሎት እንዲኖር በማድረግ ጠንካራ ተቆጣጣሪ ተቋም እንዲፈጠር ማስቻሉን አብራርተዋል። በአፍሪካ አቪዬሽን ዘርፍ ለሚስተዋሉ ችግሮች ዘላቂ እልባት ለማበጀት በጋራ መስራት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ችግሮችን ከመለየት ባለፈ ተግባራዊ የመፍትሔ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባ አሳስበዋል። ኢትዮጵያም በመስኩ ያሉ ማነቆዎች እንዲፈቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም አረጋግጠዋል።   የዓለም አቀፍ ሲቪል አቪየሽን ድርጅት የምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ሉሲ ቡግዋ በበኩላቸው፤ የአፍሪካን የአቪየሽን ትስስር ለማፋጠን ሀገራት በትብብር ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ደኅንነቱ የተጠበቀ የአቪየሽን መሠረተ ልማት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።   የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር ዋና ጸኃፊ አብድራህማን በርቴ፤ የአህጉሪቱን የበራራ ግንኙነት ለማፋጠን በርካታ ሀገራት የአፍሪካ የተቀናጀ የአየር ትራንስፖርት ገበያ የትብብር ማዕቀፍ መፈረማቸውን ገልጸዋል። ሀገራቱም የትብብር ስምምነት ማዕቀፉን ከመፈረም ባሻገር ወደ ተግባር እንዲለወጥ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።   የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ አህጉሪቱን በአቪየሽን ልማት በማስተሳሰር የሚጠበቅበትን ገንቢ ሚና እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም ከአፍሪካ የአቪየሽን ኢንዱስትሪ ተዋናዮች ጋር በመተባበር አህጉሪቱን ለማስተሳሰር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከልና የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስኬታማ ተግባራትን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
Apr 29, 2026 369
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከልና የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስኬታማ ተግባራትን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ፡፡ ቋሚ ኮሚቴው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃጸም ሪፖርትን ገምግሟል።   የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በሪፖርታቸው፤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ዓለምአቀፍ ዕውቅና ያስገኙ የወንጀል መከላከል ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል። በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ከፍተኛ ወንጀል የሚፈጽሙ አካላትን በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን በኮንትሮባንድ መከላከል፣ ቁጥጥር፣ ሕገ-ወጥ የገንዘብና አደንዛዥ ዕፅ ዝውውር የወንጀል መከላከል ዘርፍም ስኬታማ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል። በወንጀል ምርመራ፣ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር፣ የሽብር ወንጀል መከላከል ዘርፍም የማድረግ አቅምን በማሳደግ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል። በሰው ሀብት ልማትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመታጠቅም በአፍሪካና በዓለምአቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነቱ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።   ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ኮሚሽኑ ኢትዮጵያዊ መልክ እንዲላበስ፣ የዜጎችን ሰብአዊ መብት የጠበቀ የወንጀል ምርመራ እንዲያካሂድና የአሰራር አቅሙን በማሳደግ የምርመራ መዝገብ አፈጻጸሙን ማሳደግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ መንግሥታዊና ሕዝባዊ በዓላትም ያለ ምንም የጸጥታ ስጋት እንዲከበሩ ማስቻሉን ተናግረዋል። የቋሚ ኮሚቴው አባላት የኮሚሽኑን የዕቅድ አፈፃጸም ሪፖርት በመገምገም በሂደቱ የታዩ ጥንካሬና ክፍተቶችን በአስተያየትና ጥያቄ መልክ አቅርበዋል። በዚህም የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በወንጀል መከላከልና የወንጀል ተጠያቂነትን ለማስፈን የተገኙ ስኬቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።   የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል መላኩ ፈንታ በኮሚሽኑ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሚያደርጉና አለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያሳድጉ ዘመኑ የደረሰበት ቴክኖሎጂዎች መተግበራቸውን ተናግረዋል። የስማርት ፖሊስ ስቴሽን ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ ተግባራዊ መደረጉን ገልጸው፤ የቴክኖሎጂውን ተደራሽነት ለማስፋፋት እየተሰራ ነው ብለዋል። ማህበረሰቡ ወንጀሎችን መጠቆም የሚችልበት ቴክኖሎጂ ተግባራዊ በመደረጉ በሺዎች የሚቆጠሩ ጥቆማዎች መቅረባቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የትራፊክ አደጋን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በቴክኖሎጂ የታገዙ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ጠቅሰዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ እፀገነት መንግሥቱ፤ ፌዴራል ፖሊስ በወንጀል መከላከልና ተጠያቂነትን በማስፈን ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል። ፌዴራል ፖሊስ ተቋማዊ ግንባታንና ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የሚሰራቸውን ስራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥልና የወንጀል መከላከል ተግባራትን በማህበረሰቡ ተሳትፎ ለማጎልበት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፍ ሁነቶችና በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቁ በማድረግ ለሀገሪቱ የገጽታ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በሰው ሀብት አቅም ግንባታና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ለውጦችን በማስቀጠል የወንጀል ተጠያቂነት የማስፈንና የወንጀል መከላከል ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰላምና ደኅንነት አስተማማኝ በሆነ ሁኔታ ለመጠበቅ የጀመራቸውን የሪፎርም ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የፓርቲዎች ክርክርና የምረጡኝ ቅስቀሳ የፖሊሲ አማራጮች ላይ ማተኮር አለበት - ምሁራን
Apr 30, 2026 160
ወልቂጤ፤ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡-የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክርና የምረጡኝ ቅስቀሳ ለሃገር በሚበጁ ሃሳቦችና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ማተኮር እንዳለበት ምሁራን ገለጹ፡፡ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሔደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ክልላዊና ሃገራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሀን፣ በጎዳና ላይ እና በተለያዩ አማራጮች ክርክርና የምረጡን ቅስቀሳ እያካሄዱ ነው። ፓርቲዎችና የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች በመገናኛ ብዙሃን አማራጭ ሃሳቦችን ማቅረባቸው ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ምሁራኑ አመልክተዋል፡፡ የተፎካካሪ ፓርቲዎቹ ክርክርና የምረጡኝ ቅስቀሳ ለሀገር በሚበጁ ሃሳቦችና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ማተኮር እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ክርክሮችና ቅስቀሳዎች ካለፉት ምርጫዎች በተሻለና ህዝብን ባከበረ መልኩ እየተካሄደ ነው። በምርጫ ቅስቀሳው ወቅት ለሀገር በሚበጁ ሀሳቦችና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ማተኮር አለባቸው ብለዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ኢንጂነር ቀነኒ ኤልያስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በመገናኛ ብዙሃን እየተደረገ ያለው የምርጫ ቅስቀሳና ክርክር ፓርቲዎቹ የያዙትን አማራጭ ሃሳብ ለመራጩ ህዝብ ግልፅ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲዎቹ ልማትና አብሮነት ላይ ያተኮረ የፖሊሲ አማራጮችን በማቅረብ ለሀገር በሚጠቅሙ ሃሳቦች ላይ ማተኮር እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡ ፓርቲዎች በቅድመ ምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ሀገርን ቀዳሚ የሚያደርጉና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ተጨባጭ ሀሳቦችን ማንሳት እንዳለባቸው የጠቀሱት ደግሞ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ እድሜዓለም ተመስገን ናቸው። የወለጋ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ስለሺ ታመነ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ፓርቲዎቹ ኢትዮጵያን መንግስት መስርተው ሊመሯት የሚችሉት አንድነቷና ሰላሟ ሲጠበቅ መሆኑን በመገንዘብ ፍፁም መከባበርና መቻቻልን መርህ አድርገው ሊንቀሳቀሱ ይገባል ብለዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ለሀገር ዕድገትና ልማት ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል-ተማሪዎች
Apr 30, 2026 153
ሐረር፤ሚያዝያ 22/2018(ኢዜአ)፦ ለሀገር ዕድገትና ልማት ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች ተናገሩ። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀናል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ ልዩ የመመዝገቢያ ድረ ገጽን በመጠቀም ምዝገባ ማካሄዳቸውንም ገልጸዋል። ከተማሪዎቹ መካከል በኮሌጁ የ3ኛ ዓመት ተማሪ መክሊት ሻውል እንዳለችው ምርጫ ቦርድ ባዘጋጀላቸው ልዩ የመመዝገቢያ ድረ ገጽን በመጠቀም ይበጀኛል የምትለውን ፓርቲ ለመምረጥ መመዝገቧን ገልጻለች። "ለምርጫ ስመዘገብ የመጀመሪያዬ ነው" ያለችው ተማሪዋ ለሀገር ይጠቅማል፤እኔንም ይወክለኛል የምለውን ፓርቲ እመርጣለሁ ብላለች። ሌላው የኮሎጁ የ3ኛ ዓመት የላቦራቶሪ ቴክኒሺያን ተማሪ ሙርቴሳ ዲኒ ይህንን እድል ተማሪዎች በማግኘታችንም እድለኛ ነን ብሏል። የአራተኛ ዓመት የፋርማሲ ተማሪ አሚራ መኪ በበኩሏ፥ ለሀገር ዕድገትና ልማት ይበጃል የምትለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቷን ተናግራለች። በኮሌጁ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንትና የአምስተኛ ዓመት የህክምና ሳይንስ ተማሪ አድናን አብዱሰላም ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳና ልዩ የመመዝገቢያ ድረ ገጽ በመጠቀም ተማሪዎች ባሉ አማራጮች ሁሉ እንዲመዘገቡ እያደረግን እንገኛለን ብሏል። በአሁኑ ውቅትም ልዩ የመመዝገቢያ ድረ ገጽን በመጠቀም ተማሪዎች እየተመዘገቡ እንደሚገኙም ተናግሯል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ለጠቅላላ ምርጫው የፖሊሲ አማራጫችንን ለህዝቡ በነጻነት እያስተዋወቅን ነው- የፖለቲካ ፓርቲዎች
Apr 29, 2026 1350
ሚዛን አማን፣ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ):-በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖሊሲና ፕሮግራማቸውን ለህዝቡ በነጻነት እያስተዋወቁ መሆናቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ኢዜአ ያነጋገራቸው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የፖሊሲ አማራጫቸውን በነጻነት እያስተዋወቁ መሆኑን ገልጸዋል። የቤንች ሸኮ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ የቤንች ሸኮ ዞን ፀሐፊ መምህር ብርሃኑ ገብረመድኅን በምርጫ ሂደቱ በሰለጠነ መንገድ ለሕዝብ አማራጭ ሀሳባቸውን እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።   የምርጫ ሕግና ሥርዓትን ጠብቀን የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም ሕዝቡ ማኒፌስቷችንን በግልጽ እንዲረዳው እያደረግን ነው ብለዋል። በቅስቀሳ ወቅት ወደ ሕዝቡ ቀርቦ ሀሳብን ማካፈልና የፓርቲ አቋምን ማሳወቅ መራጮች በምርጫ ጊዜ ሳይቸገሩ የሚፈልጉትን ሀሳብ የያዘ ፓርቲ እንዲመርጡ ያስችላል ሲሉም አክልዋል። ከሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፓርቲ የካፋ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ሕብረት ሰብሳቢ አቶ ቦጋለ ኃይሌ በበኩላቸው፥ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተፈጠረውን አስቻይ ሁኔታ በመጠቀም ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።   በየምርጫ ክልሉ በመንቀሳቀስ የቅስቀሳ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጸው፥ የፓርቲው እጩዎችም ከኅብረተሰቡ ጋር በቅርበት የመወያየትና ሀሳባቸውን የመሸጥ ተግባርን እያከናወኑ ነው ብለዋል። በሚዲያ እየተደረጉ ያሉ የክርክር መድረኮች ለመራጩ ህዝብ በሀሳብ የበላይነት መንግስት መመስረት ላይ የበኩሉን እንዲወጣ መሰረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመዋል። በቅስቀሳ እና በክርክር መድረኮች የምርጫ ህጉን አክብረው ማኒፌስቷቸውን ለመራጮች በማድረስና የፓርቲያቸውን አቋም በማንጸባረቅ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።   ከትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ የእናት ፓርቲ ሚዛን ማዕከል ፀሐፊ አቶ ወንድማገኝ ወልደጊዮርጊስ፤ የምርጫውን ፍትኃዊነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ለተግባራዊነቱም የምርጫ ህጉን ተከትለው የፖለቲካ አቋማቸውን ለህዝቡ እያሰረጹ መሆኑን ገልጸዋል። የቅስቀሳና ክርክር መርሐ ግብሮቹ ህዝቡ ለሀገር እድገት የተሻለ አማራጭ ሀሳብ የያዘ ፓርቲ በመለየት በምርጫ ጊዜ ሳይቸገር ለመምረጥ የሚያስችሉ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ ለመውሰድ ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያስመሰከረ ነው 
Apr 29, 2026 852
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ ለመውሰድ ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያስመሰከረ መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቅን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ ማሩ ጃኔ፤ የጋራ ምክር ቤቱ በከተማዋ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙርያ ከከተማው አስተዳደር ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደትም ምክር ቤቱ የመዲናዋ ነዋሪዎች የመራጭነት ካርድ እንዲወስዱ በተለያየ መንገድ ግንዛቤ ሲያስጨብጥ መቆየቱን ተናግረዋል። ምርጫውን በተመለከተም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውጤታማ ውይይቶች መደረጋቸውን አንስተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ የምርጫ ካርድ በማውጣት ያሳየው ከፍተኛ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነትም ህብረተሰቡ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት በተግባር ያስመሰከረ መሆኑን ተናግረዋል። የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቅ የምርጫው መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አለመሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ሁሉም አካላት በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ምክር ቤቱም ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ ዘሪሁን ኮርሜ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ ምርጫው ፍትሐዊ፣ ነጻ እና ሰላማዊ እንዲሆን የሚጠበቅበትን ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን በማድረግ የጋራ ተግባቦትን እየፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅም ከምርጫ ቦርድ ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። በተጨማሪም በምርጫው የህብረተሰቡ ንቃተ ህሊና እንዲዳብር የተደራጀ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ምክር ቤቱ ለምርጫው ስኬታማነት ሚናውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ቀጣናዊ የሽምግልና ጥረቶች በጠንካራ ፖለቲካዊ መሰረት ላይ ሊገነቡ ይገባል - ኢጋድ 
Apr 28, 2026 2197
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚደረጉ የሽምግልና ጥረቶች በጠንካራ ፖለቲካዊ መሰረት ላይ ሊገነቡ ይገባል ሲሉ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ጸሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለጹ። የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሽምግልና ምክክር ጉባኤ ዛሬ በኬንያ ናይሮቢ መካሄድ ጀምሯል። ጉባኤው እየተካሄደ የሚገኘው “ሽምግልናን በተከፋፈለ ዓለም ውስጥ በአዲስ መልክ መቃኘት፦ የአፍሪካ ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ፈተናዎች” በሚል መሪ ሀሳብ ነው። የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የኬንያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቪዲ እና አጋር አካላት በጉባኤው ላይ ተገኝተዋል።   ውይይቱ በፍጥነት እየተቀያየረ ባለው ዓለም አቀፋዊ ሥርዓት ውስጥ የሽምግልና የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ያተኮረ ነው። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ለኢጋድ ሽምግልና እንደ አማራጭ የሚታይ የዲፕሎማሲ ዘርፍ ሳይሆን፣ ተቋሙ በዋነኛነት ሊወጣው የሚገባው ቀዳሚ የፖለቲካ ግዴታ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል። የሽምግልና ጥረቶች ፍሬ ማፍራት ወይም አለማፍራት፣ ተቋሙ ያለውን የጋራ አመራር ብቃትና ተቋማዊ ክብደት የሚፈትን ትልቅ አጋጣሚ ነው ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ የሚደረጉ የሽምግልና ጥረቶች ስኬታማ እንዲሆኑ ከተበታተነ አካሄድ ወጥተው፣ በአንድ ወጥ ስትራቴጂያዊ መሪ ዕቅድ የሚመሩና የጠነከረ ፖለቲካዊ መሰረት ያላቸው ሊሆኑ እንደሚገባም አንስተዋል። ማንኛውም የዲፕሎማሲ ድርድር በግጭት ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ህይወትና ደህንነት ዋና ማዕከሉ ሊያደርግ ይገባልም ነው ያሉት። በፍጥነት እየተቀየረ ካለው የዓለም ስርዓት አኳያ ሽምግልናን በአዲስ መልክ መቃኘት እንደሚያስፈልግም አንስተዋል። የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሽምግልና ምክክር ጉባኤ እስከ ነገ እንደሚቆይ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬታሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዜጎች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ሊጠቀሙ ይገባል
Apr 28, 2026 1338
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ዜጎች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን መጠቀም እንደሚጠበቅባቸው የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ሲያካሄድ ቆይቶ ተጠናቋል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት ሲሆን በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የተመዘገቡ መራጮች በአካል በመገኘት ድምፅ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው መረጃ ከ50 ሚሊዮን 514 ሺህ በላይ መራጮች ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ወስደዋል። በተጨማሪም ለሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ በዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ ተማሪዎችና በካምፕ ለሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በልዩ ሁኔታ እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በመመዝገብ የምርጫ ካርዳቸውን መውሰድ ይችላሉ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፤ ምርጫ ዜጎች ዴሞክራሲያዊና ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን የሚጠቀሙበት የአደባባይ መድረክ ነው ብለዋል። ለዚህም ዜጎች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስክ ልማትና ዕድገትን የሚያፋጥን ጠንካራ መንግስት ለመመስረት በምርጫ ሂደት የነቃ ተሳትፎ የማድረግ ሀገራዊ ግዴታ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የምርጫ ሂደትም በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ ጠንካራ መንግሥት ለመመስረት ዜጎች ይበጀኛል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ የሚሰጡበት የጋራ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በግንቦት 2018 ዓ.ም ለምታካሂደው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሕዊነትም የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ዜጎች የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በመጠቀም ይበጀኛል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀት እንዳለባቸው አንስተዋል።
የኢትዮጵያና የሞዛምቢክ ግንኙነት በነፃነት ትግል ወቅት በደም የተፈተነ ነው
Apr 28, 2026 1274
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያና የሞዛምቢክ ግንኙነት በነፃነት ትግል ወቅት በደም የተፈተነ ታሪካዊ ወንድማማችነት ነው ሲሉ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ ገለጹ። በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት የሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ፣ በዛሬው ዕለት በኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። ፕሬዝዳንቱና ከፍተኛ የልዑካን ቡድናቸው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ሲደርሱ በሚኒስትሯ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን፤ ከኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋርም ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት ሚኒስትሯ የኢትዮጵያና የሞዛምቢክ ግንኙነት በነፃነት ትግል ወቅት በደም የተፈተነ ታሪካዊ ወንድማማችነት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ለሞዛምቢክ ነፃነት ያበረከተችው አስተዋጽኦ የፓን አፍሪካኒዝም መርህ ቀዳሚ መገለጫ መሆኑን አስታውሰዋል። አሁን ያለውን ታሪካዊ ትስስር ወደ ላቀ ስልታዊ ወታደራዊ ትብብር ለማሸጋገርም ግልፅ ፍላጎትና ዕቅድ መኖሩን አመልክተዋል። ፕሬዝዳንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለሞዛምቢክ ሉዓላዊነትና ነፃነት ያበረከተችውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማስታወስ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ያለውን የላቀ የውጊያ ብቃትና የዝግጁነት ደረጃ ያደነቁት ፕሬዝዳንቱ፣ ይህ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ወታደራዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ገልፀዋል። ፕሬዝዳንቱ በቆይታቸውም ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር በወቅታዊ ቀጠናዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብር ስትራቴጂዎች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። ይህ የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ከማጠናከሩ ባለፈ ለአህጉራዊ ሰላምና ደህንነት መጠናከር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው መገለጹን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ረቂቅ አዋጁ በቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለመመከትና ለመጠበቅ ያስችላል
Apr 28, 2026 1119
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፡- የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጅ በቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን በመመከት ሉዓላዊነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ እንዲቻል ያደርጋል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ምህረቱ ሻንቆ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 17ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ለዝርዝር ዕይታ ለውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ምህረቱ ሻንቆ (ዶ/ር) የረቂቅ አዋጁን አስፈላጊነት አብራርተዋል። በዚህም በቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚነጣጠሩ የሳይበር ጥቃቶች በሀገሪቷ ምጣኔ ሀብት፣ ማኅበራዊ መስተጋብር፣ ብሔራዊ ደህንነት፣ ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ሉዓላዊነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ በመሆናቸው ረቂቅ አዋጁን ማዘጋጀት ማስፈለጉን ገልጸዋል። በተጨማሪም በቁልፍ መሠረተ ልማቶች እና መሠረተ ልማቶቹ በሚይዟቸው ኢንፎርሜሽኖችና ዳታዎች ላይ እየጨመሩ የመጡ የሳይበር ደህንነት ተጋላጭነቶችና ሥጋቶችን መቀነስና መከላከል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነም አስረድተዋል። ሥጋትን መሠረት ያደረገ የቁልፍ መሠረተ ልማቶች ልየታ በማድረግ የሀገሪቷን ሀብት አቀናጅቶ ለመምራት የሚያስችል የሳይበር ደህንነት ጥበቃና ቁጥጥር ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱም ነው ብለዋል። ለቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ጥበቃ በባለድርሻ አካላት መካከል የተቀናጀ፣ ውጤታማና ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እና የሳይበር ክስተቶችን ለማጋራትና ለመግታት የሚያስችል ሥርዓት መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ ስለመገኘቱም አንስተዋል። ውስብስብ፣ ተለዋዋጭ እና ከፍተኛ የሆነ ውድድር ባለበት የሳይበር ምህዳር ውስጥ የሚደረግ የሳይበር ደህንነትን የማረጋገጥ ተግባር ከፍተኛ የሆነ የካፒታል ዐቅምን የሚጠይቅ በመሆኑ ነው ብለዋል። ለቁልፍ መሠረተ ልማቶች ጥበቃ የሚውል አስተማማኝ ሀገራዊ የፋይናንስ ዐቅም መፈጠር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ረቂቅ አዋጁ እንዲዘጋጅ ተደርጓል ነው ያሉት። ቁልፍ መሠረተ ልማቶችን በሚያስተዳድሩና የሳይበር ደህንነት ጥበቃን በሚያደርጉ አካላት ላይ ግልጽ ኃላፊነትና ተጠያቂነት መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ ስለመገኘቱም አክለዋል። ምክር ቤቱ በስብሰባው፤ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ መካከል የተደረገ የብድር ስምምነት እና በኢፌዴሪ መንግሥት እና በአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ማኅበር መካከል የተደረገ የብድር ስምምነት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አፅድቋል።
ፖለቲካ
የፓርቲዎች ክርክርና የምረጡኝ ቅስቀሳ የፖሊሲ አማራጮች ላይ ማተኮር አለበት - ምሁራን
Apr 30, 2026 160
ወልቂጤ፤ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡-የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክርና የምረጡኝ ቅስቀሳ ለሃገር በሚበጁ ሃሳቦችና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ማተኮር እንዳለበት ምሁራን ገለጹ፡፡ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሔደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ክልላዊና ሃገራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሀን፣ በጎዳና ላይ እና በተለያዩ አማራጮች ክርክርና የምረጡን ቅስቀሳ እያካሄዱ ነው። ፓርቲዎችና የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች በመገናኛ ብዙሃን አማራጭ ሃሳቦችን ማቅረባቸው ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ምሁራኑ አመልክተዋል፡፡ የተፎካካሪ ፓርቲዎቹ ክርክርና የምረጡኝ ቅስቀሳ ለሀገር በሚበጁ ሃሳቦችና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ማተኮር እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ክርክሮችና ቅስቀሳዎች ካለፉት ምርጫዎች በተሻለና ህዝብን ባከበረ መልኩ እየተካሄደ ነው። በምርጫ ቅስቀሳው ወቅት ለሀገር በሚበጁ ሀሳቦችና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ማተኮር አለባቸው ብለዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ኢንጂነር ቀነኒ ኤልያስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በመገናኛ ብዙሃን እየተደረገ ያለው የምርጫ ቅስቀሳና ክርክር ፓርቲዎቹ የያዙትን አማራጭ ሃሳብ ለመራጩ ህዝብ ግልፅ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ፓርቲዎቹ ልማትና አብሮነት ላይ ያተኮረ የፖሊሲ አማራጮችን በማቅረብ ለሀገር በሚጠቅሙ ሃሳቦች ላይ ማተኮር እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡ ፓርቲዎች በቅድመ ምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ሀገርን ቀዳሚ የሚያደርጉና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ተጨባጭ ሀሳቦችን ማንሳት እንዳለባቸው የጠቀሱት ደግሞ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ እድሜዓለም ተመስገን ናቸው። የወለጋ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ስለሺ ታመነ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ፓርቲዎቹ ኢትዮጵያን መንግስት መስርተው ሊመሯት የሚችሉት አንድነቷና ሰላሟ ሲጠበቅ መሆኑን በመገንዘብ ፍፁም መከባበርና መቻቻልን መርህ አድርገው ሊንቀሳቀሱ ይገባል ብለዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ለሀገር ዕድገትና ልማት ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል-ተማሪዎች
Apr 30, 2026 153
ሐረር፤ሚያዝያ 22/2018(ኢዜአ)፦ ለሀገር ዕድገትና ልማት ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች ተናገሩ። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀናል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ ልዩ የመመዝገቢያ ድረ ገጽን በመጠቀም ምዝገባ ማካሄዳቸውንም ገልጸዋል። ከተማሪዎቹ መካከል በኮሌጁ የ3ኛ ዓመት ተማሪ መክሊት ሻውል እንዳለችው ምርጫ ቦርድ ባዘጋጀላቸው ልዩ የመመዝገቢያ ድረ ገጽን በመጠቀም ይበጀኛል የምትለውን ፓርቲ ለመምረጥ መመዝገቧን ገልጻለች። "ለምርጫ ስመዘገብ የመጀመሪያዬ ነው" ያለችው ተማሪዋ ለሀገር ይጠቅማል፤እኔንም ይወክለኛል የምለውን ፓርቲ እመርጣለሁ ብላለች። ሌላው የኮሎጁ የ3ኛ ዓመት የላቦራቶሪ ቴክኒሺያን ተማሪ ሙርቴሳ ዲኒ ይህንን እድል ተማሪዎች በማግኘታችንም እድለኛ ነን ብሏል። የአራተኛ ዓመት የፋርማሲ ተማሪ አሚራ መኪ በበኩሏ፥ ለሀገር ዕድገትና ልማት ይበጃል የምትለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቷን ተናግራለች። በኮሌጁ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንትና የአምስተኛ ዓመት የህክምና ሳይንስ ተማሪ አድናን አብዱሰላም ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳና ልዩ የመመዝገቢያ ድረ ገጽ በመጠቀም ተማሪዎች ባሉ አማራጮች ሁሉ እንዲመዘገቡ እያደረግን እንገኛለን ብሏል። በአሁኑ ውቅትም ልዩ የመመዝገቢያ ድረ ገጽን በመጠቀም ተማሪዎች እየተመዘገቡ እንደሚገኙም ተናግሯል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ለጠቅላላ ምርጫው የፖሊሲ አማራጫችንን ለህዝቡ በነጻነት እያስተዋወቅን ነው- የፖለቲካ ፓርቲዎች
Apr 29, 2026 1350
ሚዛን አማን፣ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ):-በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፖሊሲና ፕሮግራማቸውን ለህዝቡ በነጻነት እያስተዋወቁ መሆናቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ኢዜአ ያነጋገራቸው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የፖሊሲ አማራጫቸውን በነጻነት እያስተዋወቁ መሆኑን ገልጸዋል። የቤንች ሸኮ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ የቤንች ሸኮ ዞን ፀሐፊ መምህር ብርሃኑ ገብረመድኅን በምርጫ ሂደቱ በሰለጠነ መንገድ ለሕዝብ አማራጭ ሀሳባቸውን እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።   የምርጫ ሕግና ሥርዓትን ጠብቀን የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም ሕዝቡ ማኒፌስቷችንን በግልጽ እንዲረዳው እያደረግን ነው ብለዋል። በቅስቀሳ ወቅት ወደ ሕዝቡ ቀርቦ ሀሳብን ማካፈልና የፓርቲ አቋምን ማሳወቅ መራጮች በምርጫ ጊዜ ሳይቸገሩ የሚፈልጉትን ሀሳብ የያዘ ፓርቲ እንዲመርጡ ያስችላል ሲሉም አክልዋል። ከሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፓርቲ የካፋ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ሕብረት ሰብሳቢ አቶ ቦጋለ ኃይሌ በበኩላቸው፥ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተፈጠረውን አስቻይ ሁኔታ በመጠቀም ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።   በየምርጫ ክልሉ በመንቀሳቀስ የቅስቀሳ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጸው፥ የፓርቲው እጩዎችም ከኅብረተሰቡ ጋር በቅርበት የመወያየትና ሀሳባቸውን የመሸጥ ተግባርን እያከናወኑ ነው ብለዋል። በሚዲያ እየተደረጉ ያሉ የክርክር መድረኮች ለመራጩ ህዝብ በሀሳብ የበላይነት መንግስት መመስረት ላይ የበኩሉን እንዲወጣ መሰረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመዋል። በቅስቀሳ እና በክርክር መድረኮች የምርጫ ህጉን አክብረው ማኒፌስቷቸውን ለመራጮች በማድረስና የፓርቲያቸውን አቋም በማንጸባረቅ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።   ከትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ የእናት ፓርቲ ሚዛን ማዕከል ፀሐፊ አቶ ወንድማገኝ ወልደጊዮርጊስ፤ የምርጫውን ፍትኃዊነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ለተግባራዊነቱም የምርጫ ህጉን ተከትለው የፖለቲካ አቋማቸውን ለህዝቡ እያሰረጹ መሆኑን ገልጸዋል። የቅስቀሳና ክርክር መርሐ ግብሮቹ ህዝቡ ለሀገር እድገት የተሻለ አማራጭ ሀሳብ የያዘ ፓርቲ በመለየት በምርጫ ጊዜ ሳይቸገር ለመምረጥ የሚያስችሉ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ ለመውሰድ ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያስመሰከረ ነው 
Apr 29, 2026 852
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ ለመውሰድ ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያስመሰከረ መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቅን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ ማሩ ጃኔ፤ የጋራ ምክር ቤቱ በከተማዋ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙርያ ከከተማው አስተዳደር ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደትም ምክር ቤቱ የመዲናዋ ነዋሪዎች የመራጭነት ካርድ እንዲወስዱ በተለያየ መንገድ ግንዛቤ ሲያስጨብጥ መቆየቱን ተናግረዋል። ምርጫውን በተመለከተም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውጤታማ ውይይቶች መደረጋቸውን አንስተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ የምርጫ ካርድ በማውጣት ያሳየው ከፍተኛ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነትም ህብረተሰቡ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት በተግባር ያስመሰከረ መሆኑን ተናግረዋል። የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቅ የምርጫው መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አለመሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ሁሉም አካላት በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ምክር ቤቱም ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ ዘሪሁን ኮርሜ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ ምርጫው ፍትሐዊ፣ ነጻ እና ሰላማዊ እንዲሆን የሚጠበቅበትን ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን በማድረግ የጋራ ተግባቦትን እየፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅም ከምርጫ ቦርድ ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። በተጨማሪም በምርጫው የህብረተሰቡ ንቃተ ህሊና እንዲዳብር የተደራጀ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ምክር ቤቱ ለምርጫው ስኬታማነት ሚናውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ቀጣናዊ የሽምግልና ጥረቶች በጠንካራ ፖለቲካዊ መሰረት ላይ ሊገነቡ ይገባል - ኢጋድ 
Apr 28, 2026 2197
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚደረጉ የሽምግልና ጥረቶች በጠንካራ ፖለቲካዊ መሰረት ላይ ሊገነቡ ይገባል ሲሉ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ጸሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለጹ። የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሽምግልና ምክክር ጉባኤ ዛሬ በኬንያ ናይሮቢ መካሄድ ጀምሯል። ጉባኤው እየተካሄደ የሚገኘው “ሽምግልናን በተከፋፈለ ዓለም ውስጥ በአዲስ መልክ መቃኘት፦ የአፍሪካ ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ፈተናዎች” በሚል መሪ ሀሳብ ነው። የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የኬንያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቪዲ እና አጋር አካላት በጉባኤው ላይ ተገኝተዋል።   ውይይቱ በፍጥነት እየተቀያየረ ባለው ዓለም አቀፋዊ ሥርዓት ውስጥ የሽምግልና የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ያተኮረ ነው። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ለኢጋድ ሽምግልና እንደ አማራጭ የሚታይ የዲፕሎማሲ ዘርፍ ሳይሆን፣ ተቋሙ በዋነኛነት ሊወጣው የሚገባው ቀዳሚ የፖለቲካ ግዴታ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል። የሽምግልና ጥረቶች ፍሬ ማፍራት ወይም አለማፍራት፣ ተቋሙ ያለውን የጋራ አመራር ብቃትና ተቋማዊ ክብደት የሚፈትን ትልቅ አጋጣሚ ነው ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ የሚደረጉ የሽምግልና ጥረቶች ስኬታማ እንዲሆኑ ከተበታተነ አካሄድ ወጥተው፣ በአንድ ወጥ ስትራቴጂያዊ መሪ ዕቅድ የሚመሩና የጠነከረ ፖለቲካዊ መሰረት ያላቸው ሊሆኑ እንደሚገባም አንስተዋል። ማንኛውም የዲፕሎማሲ ድርድር በግጭት ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ህይወትና ደህንነት ዋና ማዕከሉ ሊያደርግ ይገባልም ነው ያሉት። በፍጥነት እየተቀየረ ካለው የዓለም ስርዓት አኳያ ሽምግልናን በአዲስ መልክ መቃኘት እንደሚያስፈልግም አንስተዋል። የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሽምግልና ምክክር ጉባኤ እስከ ነገ እንደሚቆይ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬታሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዜጎች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ሊጠቀሙ ይገባል
Apr 28, 2026 1338
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ዜጎች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን መጠቀም እንደሚጠበቅባቸው የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ሲያካሄድ ቆይቶ ተጠናቋል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት ሲሆን በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የተመዘገቡ መራጮች በአካል በመገኘት ድምፅ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው መረጃ ከ50 ሚሊዮን 514 ሺህ በላይ መራጮች ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ወስደዋል። በተጨማሪም ለሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ በዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ ተማሪዎችና በካምፕ ለሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በልዩ ሁኔታ እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በመመዝገብ የምርጫ ካርዳቸውን መውሰድ ይችላሉ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፤ ምርጫ ዜጎች ዴሞክራሲያዊና ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን የሚጠቀሙበት የአደባባይ መድረክ ነው ብለዋል። ለዚህም ዜጎች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስክ ልማትና ዕድገትን የሚያፋጥን ጠንካራ መንግስት ለመመስረት በምርጫ ሂደት የነቃ ተሳትፎ የማድረግ ሀገራዊ ግዴታ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የምርጫ ሂደትም በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ ጠንካራ መንግሥት ለመመስረት ዜጎች ይበጀኛል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ የሚሰጡበት የጋራ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በግንቦት 2018 ዓ.ም ለምታካሂደው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሕዊነትም የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ዜጎች የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በመጠቀም ይበጀኛል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀት እንዳለባቸው አንስተዋል።
የኢትዮጵያና የሞዛምቢክ ግንኙነት በነፃነት ትግል ወቅት በደም የተፈተነ ነው
Apr 28, 2026 1274
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያና የሞዛምቢክ ግንኙነት በነፃነት ትግል ወቅት በደም የተፈተነ ታሪካዊ ወንድማማችነት ነው ሲሉ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ ገለጹ። በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት የሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ፣ በዛሬው ዕለት በኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። ፕሬዝዳንቱና ከፍተኛ የልዑካን ቡድናቸው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ሲደርሱ በሚኒስትሯ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን፤ ከኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋርም ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት ሚኒስትሯ የኢትዮጵያና የሞዛምቢክ ግንኙነት በነፃነት ትግል ወቅት በደም የተፈተነ ታሪካዊ ወንድማማችነት መሆኑን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ለሞዛምቢክ ነፃነት ያበረከተችው አስተዋጽኦ የፓን አፍሪካኒዝም መርህ ቀዳሚ መገለጫ መሆኑን አስታውሰዋል። አሁን ያለውን ታሪካዊ ትስስር ወደ ላቀ ስልታዊ ወታደራዊ ትብብር ለማሸጋገርም ግልፅ ፍላጎትና ዕቅድ መኖሩን አመልክተዋል። ፕሬዝዳንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለሞዛምቢክ ሉዓላዊነትና ነፃነት ያበረከተችውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማስታወስ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ያለውን የላቀ የውጊያ ብቃትና የዝግጁነት ደረጃ ያደነቁት ፕሬዝዳንቱ፣ ይህ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ወታደራዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ገልፀዋል። ፕሬዝዳንቱ በቆይታቸውም ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር በወቅታዊ ቀጠናዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብር ስትራቴጂዎች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። ይህ የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ከማጠናከሩ ባለፈ ለአህጉራዊ ሰላምና ደህንነት መጠናከር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው መገለጹን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ረቂቅ አዋጁ በቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለመመከትና ለመጠበቅ ያስችላል
Apr 28, 2026 1119
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፡- የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጅ በቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን በመመከት ሉዓላዊነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ እንዲቻል ያደርጋል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ምህረቱ ሻንቆ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 17ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ለዝርዝር ዕይታ ለውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ምህረቱ ሻንቆ (ዶ/ር) የረቂቅ አዋጁን አስፈላጊነት አብራርተዋል። በዚህም በቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚነጣጠሩ የሳይበር ጥቃቶች በሀገሪቷ ምጣኔ ሀብት፣ ማኅበራዊ መስተጋብር፣ ብሔራዊ ደህንነት፣ ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ሉዓላዊነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ በመሆናቸው ረቂቅ አዋጁን ማዘጋጀት ማስፈለጉን ገልጸዋል። በተጨማሪም በቁልፍ መሠረተ ልማቶች እና መሠረተ ልማቶቹ በሚይዟቸው ኢንፎርሜሽኖችና ዳታዎች ላይ እየጨመሩ የመጡ የሳይበር ደህንነት ተጋላጭነቶችና ሥጋቶችን መቀነስና መከላከል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነም አስረድተዋል። ሥጋትን መሠረት ያደረገ የቁልፍ መሠረተ ልማቶች ልየታ በማድረግ የሀገሪቷን ሀብት አቀናጅቶ ለመምራት የሚያስችል የሳይበር ደህንነት ጥበቃና ቁጥጥር ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱም ነው ብለዋል። ለቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ጥበቃ በባለድርሻ አካላት መካከል የተቀናጀ፣ ውጤታማና ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እና የሳይበር ክስተቶችን ለማጋራትና ለመግታት የሚያስችል ሥርዓት መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ ስለመገኘቱም አንስተዋል። ውስብስብ፣ ተለዋዋጭ እና ከፍተኛ የሆነ ውድድር ባለበት የሳይበር ምህዳር ውስጥ የሚደረግ የሳይበር ደህንነትን የማረጋገጥ ተግባር ከፍተኛ የሆነ የካፒታል ዐቅምን የሚጠይቅ በመሆኑ ነው ብለዋል። ለቁልፍ መሠረተ ልማቶች ጥበቃ የሚውል አስተማማኝ ሀገራዊ የፋይናንስ ዐቅም መፈጠር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ረቂቅ አዋጁ እንዲዘጋጅ ተደርጓል ነው ያሉት። ቁልፍ መሠረተ ልማቶችን በሚያስተዳድሩና የሳይበር ደህንነት ጥበቃን በሚያደርጉ አካላት ላይ ግልጽ ኃላፊነትና ተጠያቂነት መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ ስለመገኘቱም አክለዋል። ምክር ቤቱ በስብሰባው፤ በኢፌዴሪ መንግሥት እና በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ መካከል የተደረገ የብድር ስምምነት እና በኢፌዴሪ መንግሥት እና በአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ማኅበር መካከል የተደረገ የብድር ስምምነት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አፅድቋል።
ማህበራዊ
የአምቦ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መሻሻል ከእንግልት ታድጎናል - ተገልጋዮች
Apr 30, 2026 5
አምቦ፤ ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡- የአምቦ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መሻሻል ከእንግልትና አላስፈላጊ ወጪ ታድጎናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ።   ሻምበል አንዷለም ገረመው በሰጡት አስተያየት፤ በማዘጋጃ ቤቱ አንድ ጉዳይ ለማስፈጸም የቀናት ምልልስን በመጠየቁ ሳቢያ የጊዜ ብክነት ያጋጥም ነበር ብለዋል። አሁን አገልግሎቱ የዘረጋው ፈጣን አሠራር ተደራጅተው መሬት ለመጠየቅ የመጡበትን ጉዳይ በፍጥነት ለማስፈጸም እንዳገዛቸው ተናግረዋል። የማዘጋጃ ቤቱ ቀልጣፋና ዘመናዊ ሂደትን የተከተለ አሠራር እንግልትን የቀረፈ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል፡፡ በማዘጋጃ ቤቱ የተጀመረው ዘመናዊ አገልግሎት የመጡበትን ካርታ የማውጣት ጉዳይ በአጭር ጊዜ እንዲያጠናቅቁ እንዳስቻላቸው የገለጹት ደግሞ ወርቅነሽ ዴሬሳ ናቸው።   ያዴሳ ቡልቱማ በበኩላቸው በነባሩ አሠራር መረጃ ጠፋ በሚል ባለ ጉዳይን የማጉላላት ሁኔታ እንደ ነበር አውስተው፤ አሁን አገልግሎት አሰጣጡ በመሻሻሉ ጉዳያቸውን በፍጥነት ማስፈጸማቸውን አስረድተዋል።   ማዘጋጃ ቤቱ የአገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ባለ ጉዳዮች በፍጥነት የሚስተናገዱበትን ሂደት ለማሳካት የሰው ኃይልና በግብዓት የማሟላት ሥራ መሠራቱን ያስታወቁት ደግሞ የአምቦ ከተማ አሥተዳደር ማዘጋጃ ቤት ምክትል ኃላፊ ሙሊሳ ፈዬራ ናቸው። ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በማስደገፍና መልሶ በማደራጀት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይ ለማስፈጸም ይወስድ የነበረን ምልልስ በማስቀረት ተገልጋዮች ባጠረ ጊዜ ጉዳያቸውን እንዲያጠናቅቁ መደረጉን አውስተዋል።
የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች መጠናከር አለባቸው
Apr 30, 2026 52
ጂንካ፤ ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ በንቅናቄ የተጀመረው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን አስገነዘቡ።   ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ የባሕር በር የማግኘት መብት እንዳላት በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ምስክር ከተማ ለኢዜአ አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ በአደባባይ እየተነሳ ያለው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ፤ የሀገርን ብሔራዊ ደኅንነት ከማስጠበቅ ባለፈ በቀጣናው ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማስፈን ያስችላል ብለዋል። ኢትዮጵያ ያለሕግ አግባብ በፖለቲካ ሴራ የተነጠቀችውን ወደብ መልሳ እንድታገኝ የተጀመረው በመርኅ ላይ የተመሠረተ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት መጠናከር እንዳለበት መክረዋል።   የባሕር በር አለመኖር ከሀገር ደኅንነትና ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር ስለሚያያዝ አጀንዳ ሊሆን ይገባል ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ጌታቸው ብርሃኑ ናቸው። ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የኢትዮጵያን እውነታ ከማሳወቅ ባለፈ ምሁራንን ያሳተፈ ጥምረት ፈጥሮ ሳይንሳዊ መረጃና ማስረጃዎችን መሠረት ያደረገ ሐሳብ የሚንሸራሸርበት መድረክ መፍጠር እንደሚገባም ጠቁመዋል። አጀንዳው ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የዘርፉ ምሁራንም ኅብረታቸውን በማጠናከር የሕብረተሰቡን ንቃተ-ኅሊና ማሳደግና የኢትዮጵያን እውነታ ለዓለም የሚያስገነዝቡ ሥራዎችን መሥራት አለበን ብለዋል።
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን ሹመት አጸደቀ
Apr 30, 2026 55
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡-የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን ሹመት በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል። የቦርድ አባላቱን ሹመት አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት በምክር ቤቱ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ምህረቱ ሻንቆ (ዶ/ር) ተሿሚዎቹ በትምህርት ዝግጅት እንዲሁም ባዳበሩት ክህሎት የድርጅቱን ተልእኮ ማሳካት የሚችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ብሔራዊ ጥቅምን መረዳት የሚችሉ እንዲሁም ተቋሙን ለስኬት እንደሚያበቁ የታመነባቸው መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ፦ 1፡- ብሌን ማሞ ....... የቦርድ ሰብሳቢ 2፡- ፈዲላ ቢያ ....... አባል 3፡- ተስፋዬ ዘውዴ ....... አባል 4፡- መሐመድ ካሳ ....... አባል 5፡- አፈወርቅ በደዊ ....... አባል 6፡- አስማ ረዲ ....... አባል 7፡- ዮናስ በቀለ ....... አባል 8፡- ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር ....... አባል 9፡- ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር)....... አባል ሆነው እንዲሾሙ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ምክር ቤቱ መርምሮ በአንድ ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል። ተሿሚዎችም በምክር ቤቱ ቀርበው ቃለ-መሀላ ፈጽመዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ አስቻይ ምኅዳር ፈጥሯል-አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ
Apr 30, 2026 64
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ንግድና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ለዓለም አቀፍ አልሚ ባለሃብቶች ምች ምኅዳርን ፈጥሯል። የዓለም አቀፍ አልሚ ባለሃብቶችም የኢትዮጵያን ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ በመጠቀም በተለያዩ የልማት መስኮች እንዲሰማሩ እያደረገ ይገኛል። ‎የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ 3 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት መሳብ ችላለች። በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ዕድገትና ብልፅግናን የሚያፋጥን ሰፊ የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድል ያላት ሀገር ናት። የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንትን አማራጭ ለማስፋት መንግስት የሚወስዳቸው የፖሊሲ አማራጮችም የሚደነቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢኮኖሚ ዘርፍ ልማትን ለማበረታታት የተወሰዱ የፖሊሲ ማሻሻያ ተግባራትም ኢትዮጵያን አፍሪካዊት ተመራጭ የንግድና ኢንቨስትመንት መዳረሻ ሀገር እያደረጋት መሆኑን ተናግረዋል። በኢትጵያና ፈረንሳይ መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት የበለጠ ለማስፋትም በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኝ አንስተዋል። ፈረንሳይም የሀገራቱን ትብብር የበለጠ ማጠናከር የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎችን በመደገፍ ወደ ተሻለ የዕድገት ምዕራፍ ለማሸጋገር ድጋፍ እያደረገች መሆኗን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የፈረንሳይ አልሚ ባለሃብቶች በተለያዩ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አማራጮቻቸውን እያስፋፉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን ሰፊ የንግድና ኢንቨስትመንት አማራጮቻቸውን የበለጠ እንዲያሰፉ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም የሁለቱን ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር የበለጠ በማጎልበት የጋራ ተጠቃሚነትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 9 ወራት ከ2 ሚሊየን ለሚልቁ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል
Apr 30, 2026 83
አዲስ አበባ፤ 22/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ2 ሚሊየን ለሚልቁ ዜጎች በሀገር ውስጥና በውጭ የሥራ ዕድል መፈጠሩን የኦሮሚያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ክኅሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዋሲሁን ጎልጋ ገለጹ።   ለ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ፈጠራ ሥልጠና መሰጠቱንም ገልጸዋል። ከእነዚህ መካከልም ፍላጎት ያላቸውን 2 ነጥብ 6 ሚሊየን ወጣቶች በመለየት በሥራ ዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በኩል የክኅሎት ማሳደጊያ ሥልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ለኢዜአ ተናግረዋል። ከዞን እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉትን ተጨባጭ ሁኔታዎች መሠረት በማድረግ፤ በኢንዱስትሪ፣ በግብርና እና በአገልግሎት ዘርፎች የተለዩ የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውንም አስረድተዋል።   ይህ የሥራ ዕድል ፈጠራ ሂደትም በክኅሎት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን በማድረግ ዜጎች በየመስካቸው ውጤታማ እንዲሆኑ መሠራቱን አረጋግጠዋል። በበጀት ዓመቱ 2 ሚሊየን 720 ሺህ ዜጎችን በማደራጀትና በቅጥር የሥራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱን ጠቁመው፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሀገር ውስጥ ለ2 ሚሊየን 17 ሺህ 208 ዜጎች እንዲሁም 159 ሺህ ዜጎች በውጭ ሀገራት የሥራ ስምሪት እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።   ለሥራ ዕድል ተጠቃሚዎቹ ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር አንጻርም፤ 95 ሺህ ሄክታር መሬት ለማምረቻ፣ ከ7 ሺህ በላይ የመሸጫ ሼዶች እንዲሁም ከ23 ቢሊየን ብር በላይ የፋይናንስ አቅርቦት መመቻቸቱን ተናግረዋል። ወደ ሥራ የገቡ ዜጎች ለሚያመርቷቸው ምርቶች ሰፊ የገበያ ትስስር እንዲፈጠር መደረጉን ገልጸው፤ በዚህም ውጤታማ የሆኑ 1 ሺህ 800 ኢንተርፕራይዞች ወደ ኢንቨስትመንት ደረጃ እንዲሸጋገሩ መደረጉን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የቻይና ባለሃብቶችን የንግድና ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እያሳደገ ነው
Apr 29, 2026 668
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የቻይና ባለሃብቶችን የንግድና ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እያሳደገ መሆኑን በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ። አምባሳደር ቼን ሃይ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ እና ቻይና ታሪካዊና ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው። የኢትዮ-ቻይና ታሪካዊ ግንኙነት የልማት ትብብርን በማጎልበት የሀገራቱን ሁለንተናዊ ግንኙነት እያጠናከረ እንደሚገኝም ገልጸዋል። የሀገራቱ የሁለትዮሽ የንግድና ኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ አጋርነት ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ የጋራ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። የቻይና ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የሚሰማሩባቸው አዳዲስ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎችም ከፍተኛ ዕድገት እያስመዘገቡ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም የቻይና አልሚ ባለሃብቶችን የኢንቨስትመንት በራስ መተማመን በማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የፈጠረው የኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢም አዳዲስ ዕድሎችን መጠቀም የሚሹ በርካታ የቻይና ባለሀብቶችን እየሳበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የኢትዮ-ቻይና የኢኮኖሚ ትብብርም በግብርና፣ ኢንዱስትሪና የሰው ሃብት ልማት ሶስት ወሳኝ ምሰሶዎችን ማዕከል በማድረግ በስፋት እየተሰራበት መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ፈጣን የልማትና የዕድገት አቅጣጫ የሀገራቱን ስትራቴጂክ አጋርነት በማጠናከር ከፍተኛ አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል። የቻይና ባለሃብቶች የኢትዮጵያ የንግድና የአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ተሳትፎም የኢኮኖሚ ልማትና ሽግግርን በማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ተናግረዋል። የሀገራቱ በሰው ሃብት ልማት ትብብር የአዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በክህሎት የበለፀጉ ዜጎችን በማፍራት ወሳኝ ሚና እየተወጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በሚቀጥሉት ዓመታትም የሀገራቱን የንግድና ኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ አጋርነት የበለጠ በማጠናከር የሁለትዮሽ ግንኙነትን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራ ጠቅሰዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው
Apr 29, 2026 274
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለማምጣት ያላቸውን አቅም ማጠናከር እንዳለባቸው የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ ገለፁ። "ቀጣናዊ ሰላምና ትብብር ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ዓለምአቀፍ የምርምር ጉባኤ እየተካሄደ ነው። በጉባኤው በቪዲዮ ኮንፍረንስ መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ ቀጣናውን በልማት ለማስተሳሰር በሚደረግ ጥረት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ በጥናትና ምርምር መደግፍ አለባቸው።   ለዚህም ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያሳድጉና ማህበራዊ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚያግዙ የፖሊሲ መነሻ ሀሳቦችን በጥናትና ምርምር እንዲያፈልቁ አስገንዝበዋል። በተለይም ሀገረሰባዊ እውቀቶችን በምርምር በማስደገፍ በቀጣናው ሀገራት በዘመናዊ አስተዳድር ሥርአት ውስጥ የሚካተቱበትን አቅም መፍጠር ላይ ይበልጥ ማተኮር አለባቸው ብለዋል።   የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለሀገርና ለቀጣናዊ ችግሮች መፍትሄ የሚሆኑ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ማበርከቱን ጠቅሰዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ በቀጣናው እያደረሰ ያለውን ተጽዕኖ ለመከላከል ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያከናወነችው ተግባር በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው ያሉት ደግሞ በኢትዮጵያ የግሎባል ግሪን ግሮውዝ ኢንስቲትዩት (GGGI) ተወካይ ኦኬቹኩ ዳንኤል ኦግቦናያ ናቸው። የአፍሪካ ሕብረት በ2063 የሀይል፣ የውሀ ሀብትና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አጀንዳን ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት የኢትዮጵያን ልምድ ሊቀስም ይገባል ሲሉም አመልክተዋል።   በካናዳ የዩርክ ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ፕሮፌሰር አሊ አስጋሪ ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ አቅርቦትና ለአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እድገት የሰጠችው ትኩረት የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል። በምርምር ጉባኤው በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ፣ በጤና፣ በትምህርትና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ጥናቶች በተመራማሪዎች፣ በፖሊሲ አውጪዎችና ባለሙያዎች እየቀረቡ ነው።
በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የተደገፈ የኩነቶች ምዝገባ ሥርዓትን በማጠናከር የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል 
Apr 29, 2026 212
ባህር ዳር፤ ሚያዚያ 21/2018(ኢዜአ)፦ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የኩነቶች ምዝገባ ሥርዓትን በመተግበር የተገልጋዩን እርካታ የማሳደግ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአማራ ክልል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ። ‎የክልሉ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ‎ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ያለማውን የኩነቶች መመዝገቢያ ሲስተም ዛሬ ተረክቧል። ‎‎የአገልግሎቱ ኃላፊ ወይዘሪት መዓዛ በዛብህ በርክክቡ ወቅት እንደገለጹት የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎትን ውጤታማ ለማድረግ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መጠቀም አስፈላጊ ነው። ‎‎ለዚህም ተቋሙ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለምቶ ዛሬ የተረከበው የኩነት መመዝገቢያ ሲስተም መሰረታዊ ጉዳይ ነው ብለዋል። ‎‎አሁን ላይ የለማው የኩነት መመዝገቢያ ሲስተም የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችልም ተናግረዋል። ቴክኖሎጂው ስራውን ከማቀላጠፍ ባሻገር ጥራት ያለው መረጃን ለተጠቃሚው ማህብረሰብ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያግዘው አስረድተዋል። ይህም በክልሉ በተመረጡ 477 የምዝገባ ጣቢያዎች ሲስተሙ ቀደም ብሎ ተግባራዊ ተደርጎ ሲፈተሽ መቆየቱንም አመልክተዋል። ‎በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለትራንስፖርት፣ ለወረቀት፣ ለህትመትና ሌሎች ወጪዎች ይወጣ የነበረን 11 ሚሊዮን ብር ማዳን ተችሏል ብለዋል። በቀጣይም አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ የተደገፈውን የኩነቶች ምዝገባ ስርአትን በማጠናከር የተገልጋዩን እርካታ ማሳደግ ላይ አተኩሮ እንደሚሰራ አንስተዋል። ‎‎የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በምርምርና ሌሎች ተግባራት ተወዳዳሪነትቱን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ‎ለዚህም የክልሉን ተቋማት ዲጂታላይዝድ ለማድረግ ከክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የጀመረውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። ‎‎እስካሁንም ለተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የመንግስት ተቋማት ሲስተም በማልማትና በመዘርጋት ሥራቸውን ለማቀላጠፍ የሚያስችል ሥራ መስራቱን ተናግረዋል። ‎‎የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ደመቀ ቦሩ በዩኒቨርሲቲው የለማው የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ሲስተም በዕቅድ ላይ የተመሰረተ ክልላዊ ልማት ለማካሄድና ፖሊሲና ስትራቴጂን ለማውጣት ያግዛል ብለዋል።  
የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሰራሩን በማዘመን በታላቅ የሽግግር ሂደት ላይ ይገኛል -ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Apr 29, 2026 136
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሰራሩን በቴክኖሎጂ በማዘመን በታላቅ የሽግግር ሂደት ላይ እንደሚገኝ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እያከናወነ የሚገኘውን የሪፎርም ሥራዎች ጎብኝተዋል።   ከንቲባዋ በጉብኝቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ከተማ አስተዳደሩ ለተቋም ግንባታ የሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል። ተቋማት ቀጣይነት ያለው ሥራ እንዲሰሩና የአገልግሎት አሰጣጣቸውም ዘላቂ እንዲሆን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ትልቅ ማሣያ ነው ብለዋል። ተቋሙ ከቅጣት ይልቅ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መስጠት ላይ እየሰራ መሆኑን አብራርተው፤ የደንብ ጥሰት ተፈጽሞ ሲገኝ ብቻ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ባለስልጣኑ በቴክኖሎጂ ራሱን በማዘመንና በመረጃ ላይ በመመስረት ሕግና ሥርዓትን ወደ ማስከበር መሸጋገሩን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ባለስልጣኑ ወረቀት አልባ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የከተማዋ የስማርት ሲቲ ግንባታ አንዱ አካል መሆኑን ገልጸዋል። አሰራሩን በሞባይል መተግበሪያም ጭምር በመስጠት ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ መጀመሩንም ተናግረዋል።   ማህብረሰቡ የደንብ ጥሰት ሲፈጸም ካለበት ቦታ ሆኖ ጥቆማ የሚሰጥበት ዘመናዊ አሰራር መዘርጋቱንም ጠቅሰዋል። የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሰራሩን በማዘመን በታላቅ የሽግግር ሂደት ላይ እንደሚገኝም አረጋግጠዋል።
የመንግስት ሰራተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው በቴክኖሎጂ መስክ የመወዳደር አቅማቸውን ለማሳደግ አስችሏል
Apr 29, 2026 93
ገንዳውኃ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው በቴክኖሎጂ መስክ አቅማቸውን በማሳደግ ተወዳዳሪነታቸው እንዲጨምር ማድረጉን በምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢንሼቲቭ በመላው ሀገሪቷ የተጀመረው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በቴክኖሎጂ የበቃና ተወዳዳሪ የሰው ሀይልን ለማፍራት አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። 5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመው ሀገር አቀፍ ስልጠና ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግም አበርክቶው የላቀ ነው። ስልጠናው ፕሮግራሚንግ፣ በዳታ ሳይንስ፣ በአንድሮይድና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መስኮች ዜጎች ባሉበት ቦታ በበይነ-መረብ የሚከታተሉት ነው። በምዕራብ ጎንደር ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት አቶ ብሩክ ወርቄ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው በመሆኑ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ነው። ስልጠናው የቴክኖሎጂ እውቀትንና ክህሎትን በማሳደግ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን በተግባር አረጋግጠናል ነው ያሉት። ​​በዞኑ የመተማ ወረዳ አስተዳደር ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ ሳራ ወንድሙ በበኩላቸው፤ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ዓለም ካለበት የስልጣኔ ደረጃ እኩል ለመራመድ የሚያስችል ነው ብለዋል። "አለም በቴክኖሎጂ እየተመራች ባለችበት በዚህ ወቅት፣ እኛም እንደ አንድ የመንግስት ሰራተኛ ራሳችንን ማዘመንና ማብቃት ይጠበቅብናል" ነው ያሉት። ባገኙት ስልጠና ተጠቅመውም መረጃዎችን በዲጂታል ዘዴ በመሰብሰብ፣ በማቀናበርና ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ቀልጣፋ ምላሽ ከመስጠት አንፃር አዲስ እይታ የፈጠረላቸው መሆኑን ተናግረዋል። ​በዞኑ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ አቶ ስሜነው ተላከ ፤ ስልጠናው የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግና የዳታ አያያዝ ተግባራቸውን ለማቅለል እንዳስቻላቸው አስረድተዋል። ስልጠናው የላቀ ቅልጥፍና እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ከማስቻሉም በላይ አለምአቀፍ እውቅና ያለው የምስክር ወረቀት በማግኘታቸው ተወዳዳሪነታቸው ለማሳደግ አስችሎናል ብለዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አዲስ አበባ ከተማ የሚያገናኘው መርሐ ግብር ተጠባቂ ነው 
Apr 30, 2026 89
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል። ከቀኑ 9 ሰዓት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአዲስ አበባ ከተማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ።   ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ57 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። አዲስ አበባ ከተማ በ11 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። የወቅቱ የሊጉ የዋንጫ ባለቤት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካሸነፈ መሪነቱን ያጠናክራል። አዲስ አበባ ከተማ በ22ኛ ሳምንት በቦሌ ክፍለ ከተማ 1 ለ 0 ተሸንፏል። ጨዋታውን ማሸነፍ ቡድኑ ላለመውረድ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያስገኝለታል። በሌላኛው መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከይርጋጨፌ ቡና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ57 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ይርጋጨፌ ቡና በ17 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ማሸነፍ ኢትዮ ኤሌክትሪክን በዋንጫ ፉክክሩ እንዲቆይ ያደርገዋል። ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ያሸነፈው ይርጋጨፌ ቡና ከወራጅነት ስጋት ለመላቀቅ ሶስት ነጥብ ያስፈልገዋል። ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ ቦሌ ክፍለ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ ይጫወታሉ። ቦሌ ክፍለ ከተማ በ37 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ድሬዳዋ ከተማ በ24 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቦሌ ክፍለ ከተማ ካሸነፈ ተከታታይ ሶስተኛ ድሉን ያስመዘግባል። በአንጻሩ በ22ኛ ሳምንት በይርጋጨፌ ቡና የ1 ለ 0 ሽንፈት ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል።
ነገሌ አርሲ ከፋሲል ከነማ ጋር ይጫወታሉ
Apr 30, 2026 74
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 29ኛ ሳምንት ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ነገሌ አርሲ ከፋሲል ከነማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ነገሌ አርሲ በ44 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ፋሲል ከነማ በ42 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። አዲስ አዳጊው ነገሌ አርሲ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። ፋሲል ከነማ በ28ኛ ሳምንት በመቀሌ 70 እንደርታ የ3 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዷል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል። በሌላኛው መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ ቡና በ41 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ32 ነጥብ 17ኛ ደረጃን በበመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ከቀናት በፊት በ20ኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስን 3 ለ 1 ያሸነፈው ኢትዮጵያ ቡና ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ28ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ሁለቱም ቡድኖች በድል ጉዟቸው ለመቀጠል ይፋለማሉ። ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አርባምንጭ ከተማ በ24 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ34 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። የሊጉ ግርጌ ላይ የሚገኘው አርባምንጭ ከተማ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች አላሸነፈም። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ ድል መንገድ ለመመለስ ይፋለማሉ። ሀዲያ ሆሳዕና ከመቀሌ 70 እንደርታ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። በ34 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሀዲያ ሆሳዕና ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በበኩሉ በ29 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ድል ቀንቶታል። ሀዲያ ሆሳዕና ወደ ድል ለመመለስ፣ መቀሌ 70 እንደርታ ደግሞ የማሸነፍ ጉዞውን አጠናክሮ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት ይጫወታሉ።
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን ትሮፊ 2026 የዞን 5 ውድድርን ታስተናግዳለች
Apr 29, 2026 377
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የ2026 የዓለም አቀፍ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን (IHF) ትሮፊ የዞን 5 የምስራቅ አፍሪካ ውድድር ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የኢትዮጵያ እና የምስራቅ አፍሪካ እጅ ኳስ ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ፍትህ ወልደሰንበት (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ውድድሩ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 ሀገራት መካከል ከ17 ዓመት በታች (Youth) እና ከ19 ዓመት በታች (Junior) ይደረጋል። በውድድሩ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ታንዛኒያ፣ ጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና ሱዳን ይሳተፋሉ። በሁለቱም የዕድሜ ክልል አንደኛ የሚወጡት ሀገራት ቀጥታ ለአህጉራዊው የአፍሪካ ውድድር የሚያልፉ ይሆናል። የውድድሩ ዝግጅት በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን እና በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እየተመራ ሲከናወን የቆየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ዝግጅቱ መጠናቀቁ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኖች ሆቴል ገብተው ዝግጅታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ። ቡድኑ እንደ ባለፈው ዓመት አሸናፊ በመሆን ለአፍሪካ ውድድር ለማለፍና ታሪክ ለመሥራት ዝግጁ ነው ሲል የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ በመረጃው አመልክቷል። ስፖርታዊ ሁነቱ የኢትዮጵያን የማስተናገድ አቅም የሚያሳይ መሆኑንም ገልጿል።
አካባቢ ጥበቃ
ዘንድሮ በሰሜን ሸዋ ዞን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ከ36 ሺህ ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ ችግኝ ይተከላል
Apr 30, 2026 43
ደብረ ብርሃን፤ ሚያዝያ 22/ 2018 (ኢዜአ)፡- በመጪው ክረምት በሚካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ከ36 ሺህ ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ ችግኝ እንደሚተከል የሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ አስታውቋል። ለመጪው ክረምት አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሚተከሉ 294 ሚሊየን ችግኞች እስካሁን መዘጋጀታቸውን በመምሪያው የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ቡድን መሪ ጌታነህ ተ/ማርያም ገልጸዋል።   በቀሪ ወራትም ፈጥነው የሚደርሱ ችግኞች ላይ በማተኮር የማዘጋጀት ሥራው እንደሚቀጥል ጠቁመዋል። በአጠቃላይም በመጪው ክረምት ከ36 ሺህ 260 ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ ችግኞች እንደሚተከሉ ለኢዜአ ተናግረዋል። ከአሁን በፊት የተተከሉ ችግኞች አርሶ አደሩን በእንስሳት ዕርባታና ማድለብ፣ በንብ ማነብ፣ በመኖ አቅርቦትና በሌሎች የሥራ ዘርፎች በማሰማራት ጥምር ግብርናን ለማስፋፋት ምቹ ሁኔታ ፈጥረዋል ብለዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት የለሙ 1 ሺህ 163 ተፋሰሶች የአፈር ለምነትን በማሻሻል፣ የገጸና ከርሰ ምድር ውኃን በማበልጸግና ለመስኖ ልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደጋቸውንም አክለዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ባለማነው የፍራፍሬ ችግኝ ተጠቃሚነታችን አድጓል-አርሶ አደሮች
Apr 29, 2026 103
ሃዋሳ ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ያለሙት የፍራፍሬ ችግኝ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዳሳደገላቸው በሲዳማ ክልል የሸበዲኖ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ፡፡ በሲዳማ ክልል የሸበዲኖ ወረዳ አርሶ አደሮች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያለሙት የፍራፍሬ ችግኞች አድገው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ እያስቻሉ ነው፡፡ በወረዳው የፉራ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር መሃመድ ቦጋለ እና አርሶ አደር ሄርቲሞ ሬቢሶ የቡና ችግኝ በማልማት ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡   ችግኞቹን በኩታ ገጠም በመትከል፣ የተፈጥሮ አፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀትና ለጥላ የሚሆን እንሰት በመትከል ተገቢውን እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አቮካዶን ጨምሮ ለምግብነት የሚውሉ ፍራፍሬዎችን በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ በአቮካዶ ልማት የተሳተፉት አርሶ አደር ሙሴ በቴሾ ናቸው፡፡   ላለፉት ስምንት ዓመታት ሁለት ሄክታር በሚጠጋ ማሳቸው ላይ የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸው የአቮካዶ ችግኞችን ተክለው በማልማት ምርቱን ለኢንዱስትሪ ፓርኮች እንደሚሸጡም አክለዋል። የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ጽህፈት ቤት የቡና ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለሙያ አቶ ደሞዜ ሌዳሞ እንዳሉት በወረዳው በዘንድሮው ዓመት ከ726 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የቡና ችግኝ ለመትከል ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል።   በተለይም ቡና በክላስተር በማልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰራው ስራ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ቡናን ጨምሮ ለፍራፍሬና ለምግብት ለሚውሉ ችግኞች ትኩረት መሰጠቱን የገለጹት ደግሞ የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ ናቸው፡፡   በመርሃ ግብሩ ከሚተከሉ ችግኞች መካከል 60 በመቶ የሚሆኑት ለምግብነት የሚውሉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በመርሃ ግብሩም አቮካዶ፣ አፕልና ሌሎች ፍራፍሬዎችን ጨምሮ ለእንስሳት መኖም ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል፡፡ በክልሉ ለዘንድሮ ዓመት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ322 ሚሊዮን በላይ ችግኖች የተዘጋጁ ሲሆን በቡና ችግኝ ተከላ የተጀመረው መርሃ ግብር እስከ መጪው ሃምሌ ወር እንደሚከናወንም አስረድተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራና በታዳሽ ኃይል ያስመዘገበችው ስኬት፤ የአየር ንብረት ጥበቃና ዘላቂ ዕድገት የማይነጣጠሉ መሆናቸውን በተግባር ያረጋገጠ ነው
Apr 28, 2026 404
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራና በታዳሽ ኃይል ልማት የአየር ንብረት ለውጥ እና ዘላቂ ዕድገት የማይነጣጠሉ ቋሚ አጀንዳዎች መሆናቸውን በተግባር አሳይታለች ሲሉ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል።   በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃፀም ለመገምገም ነው። የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሐፊ ክላቨር ጋቴቴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ እና በኢ-ተገማች የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተስፋና ሥጋት እያስተናገደች ነው። በአፍሪካ ቀጣይነት ያለው፣ አካታችና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ለመገንባት አህጉራዊ ለውጥና ሽግግር ያስፈልጋል ብለዋል። ኢነርጂ፣ መሠረተ ልማት ማስፋፋት፣ ከተማ ከማዘመን ባለፈ በሀገራት መካከል የእሴት ትስስር መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መቋቋም የሚያስችል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን በመግለፅ፤ ለአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ግብ መሳካት ገንቢ ሚና አለው ብለዋል። ኢትዮጵያ የደን ሽፋኗን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን መትከሏን አስታውሰው፤ በዓለም የደን ልማት ዘርፍ ከፍተኛው ኢኒሼቲቭ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ 95 በመቶ ኃይል ከታዳሽ ኃይል የሚገኝ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ወሳኝነት አለው ብለዋል። በአረንጓዴ አሻራ፣ በታዳሽ ኃይልና ከተማ ልማት የተመዘገቡ ስኬቶች ከኢትዮጵያ አልፎ ለሌሎች ሀገራት ዘላቂ ዕድገት ገንቢ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል። ኢኒሼቲቮቹ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቋቋም የውኃ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ መሰረተ ልማትን ማስፋፋት ያስችላሉ ብለዋል። አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ ግቦችን ለመፈጸም በምታደርገው ጥረት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡   የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሉክ ባሃዱር ታፓ፤ በመላው አህጉሪቱ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም በሚያስችሉ ተግባራት፣ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ፣ በዲጂታል ሽግግርና በቀጣናዊ ትስስር ላይ ቁልፍ አመራር መስጠትና ዕውቀትን ማፍሰስ እንደሚገባ አመላክተዋል። ይህ የአህጉሪቱ አቅም ውጤታማ እንዲሆን ሰፊ ኢንቨስትመንት እንደሚፈልግ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ በተለይም በጤና፣ በትምህርትና በዲጂታል ልማት ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል። ዘላቂ ልማት ያለ እኩልነትና ፍትሐዊ የፋይናንስ ሥርዓት ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል በማንሳት፤ ቀጣይነት ያለው የአየር ንብረት ፋይናንስ ሥርዓት በመዘርጋት ተጎጂዎችን መድረስ እንደሚገባም ገልጸዋል። ለዚህም አባል ሀገራት የውስጥ ሀብት አሰባሰብን ማሳደግ፣ የግሉን ዘርፍ ማበረታታትና ከአጋር አካላት ጋር በትብብር መሥራት እንዳለባቸው ፕሬዝዳንት ሉክ ባሃዱር ታፓ አሳስበዋል።
በዞኑ በመጪው ክረምት የሚተከሉ 275 ሚሊዮን ችግኞች እየተዘጋጁ ነው
Apr 28, 2026 136
መቱ ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦በኢሉአባቦር ዞን በመጪው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር የሚተከሉ 275 ሚሊዮን ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳሙ ታከለ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በተካሔዱት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እና የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ተራቁተው የነበሩ አካባቢዎች ማገገም ችለዋል።   በተጨማሪም ደርቀው የነበሩ ምንጮች መጎልበታቸውን በዘርፉ ከተመዘገቡ ውጤቶች መካከል ተጠቃሽ መሆኑንም ነው የተናገሩት ። ይህንኑ በማጠናከር በመጪው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር 275 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የቦታ ልየታ ስራ እየተካሔደ መሆኑን ገልጸዋል። በመርሐ -ግብሩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ላላቸው የችግኝ ዓይነቶች ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን ከዚህም ውስጥ የፍራፍሬ እና ለከብት መኖ የሚውሉ ችግኞችም ተጠቃሽ እንደሆኑ አንስተዋል። የችግኝ ተከላ ስራው 62 ሺ ሔክታር መሬት ላይ ይከናወናል ተብሎ እንደሚጠበቅም ነው የተገለጸው።   አቶ ደረጀ ዓለሙና አቶ ምስጋና ከበደ በኖጳ ወረዳ በችግኝ ማፍላት ስራ ላይ መሰማራት በመቻላቸው ኑሯቸውን ለመደጎም የሚያስችል ገቢ እንዳስገኘላቸው ተናግረዋል። አቶ ጥላሁን አለማየሁና ወንድሙ አሰፋ ደግሞ በግል የተለያዩ ችግኞችን በማዘጋጀትና ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ለመሆን እየሰሩ መሆኑን ነው የገለጹት። ባለፉት ዓመታት በተመሳሳይ ሁኔታ የፍራፍሬ ችግኞችን በማዘጋጀት እያቀረቡ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውሰው ለዘንድሮው ዓመትም የፓፓያ እና የአቮካዶ ችግኞችን እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት ይገባል 
Apr 28, 2026 259
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት እንደሚገባ የሕብረቱ ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃጸም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 ጎን ለጎን የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው።   የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድን ሀገር በቀል በማድረግ አካታች ዕድገትና ዘላቂ የኢኮኖሚ ሽግግርን የሚያፋጥን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ገልጸዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራትም ብሔራዊ የልማት ዕቅዶችን ከአጀንዳው ጋር በማጣጣም የበጀት ድልድልና የፖሊሲ እርምጃዎችን ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካ አጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦች የበለጸገች አህጉርን እውን ለማድረግም የአባል ሀገራት ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። የአጀንዳ 2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን በማሳካት የተሳለጠ የለውጥ ሽግግርን ለመፍጠርም ጠንካራና የተሰናሰለ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና አህጉራዊ የፖሊሲ ፍሰት ሊኖር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ለዚህም የመንግሥታት፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች በወሳኝ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ የሚኖራቸውን ትብብርና ቅንጅት የሚያበረታታ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።   የዑጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትርና ተሰናባቿ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ ቢሮ ሊቀ-መንበር ሮቢናህ ናባንጃ በበኩላቸው፤ የአፍሪካውያን ድምፅ በወሳኝ የዓለም መድረኮች ላይ መንፀባረቅ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ መድረኮች በከፍተኛ ደረጃ ከሚደረግ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ባለፈ በወሳኝ ስትራቴጂክ ሂደቶች ላይ በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ብለዋል። የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካትም ሎጂስቲክስ፣ ትራንስፖርትና መሰል የትኩረት ዘርፎች ላይ በስፋት በመሰማራት ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች ነው
Apr 28, 2026 146
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃፀም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 በትይዩ የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው። በአፍሪካ አካታች ዕድገትና ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ሽግግር ለመፍጠር ወሳኝ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድ ሀገር በቀል እንዲሆን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ተናግረዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራት ብሔራዊ የልማት ዕቅዶቻቸው ከአጀንዳው ጋር እየተጣጣመ መምጣቱን በማንሳት፤ የበጀት ድልድልና ፖሊሲዎቻቸው ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ የሰጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን በማሳካት የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ በሀገራት መካከል ያለው ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባም አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸውን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ አለባቸው
Apr 27, 2026 177
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦‎ አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸው ላይ እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከታንዛኒያ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የአፍሪካ ወሳኝ ማዕድናትን ለአረንጓዴ የኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ማዋል" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጁት የ12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ቅድመ ጉባኤ ተካሂዷል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ እንደ ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ግራናይት እና ሌሎች የከርሰ ምድር ሀብቶችን ጨምሮ የዓለምን 30 በመቶ ማዕድናትን ይዛለች፡፡ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻዋን የዓለምን ከፍተኛ የኮባልት ማዕድን የያዘች መሆኑን ገልጸው፤ ይሄውም አፍሪካን የዓለም አቀፍ የኃይል ሽግግር /Energy Transition/ ማዕከል ያደርጋታል ብለዋል፡፡ አፍሪካ ዩራኒዬምና ሌሎች የከርሰ ምድር የከበሩ ማዕድናት ባለቤት መሆኗን በመጥቀስ፤ ለዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል አቅርቦት አስተዋጽኦ ከማድረግ ባለፈ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ኒውክሌር ኃይል ልማት እያመሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አፍሪካ የከበሩ ማዕድናት ባለቤት ብትሆንም አብዛኛው በጥሬ እቃ መልክ ወደ ውጭ የሚላክ በመሆኑ የአህጉሪቱ የእርስ በእርስ ግብይት ከሁለት በመቶ እንዳማይዘል ተናግረዋል፡፡ በአህጉሪቱ የማዕድናት ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን መገንባት ቢቻል በየዓመቱ ከ24 ቢሊየን ዶላር በላይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘትና ለ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ይቻላል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ የማዕድን ፖሊሲ ለእሴት መጨመር፣ ኢንዱስትሪ ልማትና ሁሉን አቀፍ ልማት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአህጉሪቱ የተቀናጀ ቀጣናዊ ኢንዱስትሪ ለመገንባት ያለውን ፍላጎት በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አህጉራዊ የማዕድን ሀብቶችን ወደ ዘላቂ ብልጽግና መለወጥ ይገባል ብለዋል፡፡ በዚህም የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቀጣናዊ እሴት ሰንሰለትን በማጠናከር የማዕድን ጸጋዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚደረገው ጥረት ትብብሩን ማጠናከሩን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካዳሪ ሲንጎ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍና አካታች ዕድገት ለማስመዝገብ የማዕድን ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በተፈጥሮ ሀብታችን ላይ የሚኖረን ትብብርና ተሳትፎ ስትራቴጂያዊና መዳረሻ ግብ ያለው መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮት ሽግግርን ለመፈጠር በአቅም ግንባታ ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 565
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 26, 2026 158
ክልሎች፤ሚያዝያ 18 /2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር የምንቃኝበት ነው። በዚህ ሳምንትም አንኳር የክልሎች ክንውኑን የሚያሳዩ መረጃዎች ቀርበዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተም! ኢትዮጵያ የበጋ መስኖ ልማት ስራ መደባኛ ስራዋ ካደረገች ወዲህ አያሌ ለውጦች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ባለፉት ዓመታት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በእቅድ እና በቁርጠኝነት በመከናወኑ ከውጪ የሚገባ ስንዴ ቀርቷል፤ የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጥረቱም ቀጥሏል። ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚደረገው ሽግግርም ዓመቱን ሙሉ በማልማት እየታጀበ ሲሆን የአንበሳውን ድርሻ የሚይዘው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሥራ ነው። በዚህ ውስጥ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አበረታች ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በተያዘው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ወሬርሶ ማሊማ፣ በጂዳ ወረዳ ሲባ ሲርቲ እና ቂምቢቢት ወረዳ ሰገሌና ደርማሙሳ ቀበሌ በኩታ ገጠም የለማ እና በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ የስንዴ ቡቃያ አስቃኝተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፎቶ ጋር ያያዙት መልዕክትም ''ይህ የበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት በምግብ ራስን የመቻል እና የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተማችን ነው'' ይላል። ብሪክስ -- ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በባህር ዳር ከተማ ''የብሪክስ አሁናዊ አቅሞች እና የኢትዮጵያ የልማት ትብብር ትኩረቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ጉባኤ አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ በመሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑ ይታወቃል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሐመድራፊዕ አባራያ በመድረኩ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ሳትፎዋን በማሳደግ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የተደራጁ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። መድረኩም ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችላት የሁለትዮሽ ትብብር ጭምር የተካሄደበት፤ በብሪክስ ማዕቀፋ በተለይም በግብርና እና ስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና መሰል ዘርፎች ልምድ የተሰጠበትም መሆኑ ተመላክቷል። ማረም እና ማነጽ የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል እንዲሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት መሰጠቱ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነው። የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነሮች የጋራ ጉባኤ “የማረሚያ ተቋማት ለሀገር ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል ሆነው እንዲያገለግሉ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከታራሚዎች የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የመሰረታዊ ፍላጎት አቅርቦት፣ ከማረሚያ ቤት የሪፎርም ሥራዎች እንዲሁም ከማረም የማነጽ ተሃድሶ ልማት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ጉባኤው በልዩ ሁኔታ የመከረበት ነው። ኢትዮጵያ ማምረቷን ቀጥላለች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የራስን አቅም የመገንባት ታሪካዊ ጉዞ እንደቀጠለ ነው። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል "ድሬ ታምርት ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ በተዘጋጀ የአምራች ኢንዱስትሪ ኤክሲፖ ላይ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ በተደረገው ድጋፍና ክትትል እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በንቅናቄው የተዘጉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲመለሱ በማድረግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በጥራትና በስፋት እየተተኩ ነው ብለዋል። ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድም መሠረታዊ ውጤቶች ተገኝተዋል ነው ያሉት። ዘንድሮ ብቻ 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ የውጭ ሀገራት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት መዘጋጀታቸውም ተገልጿል። ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል በኢትዮጵያ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ውኃ የህልውና ጉዳይ ነው። በእርግጥ ለፍጡራን ሁሉ ውኃ ህይወት ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ግን ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል። በሳምነቱም በአፋር ክልል ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የአይሳኢታ አፋምቦ የብዙሃን መንደር እና የአይሳኢታ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተከናወነው ልማት የህብረተሰቡን ጥያቄዎች በተግባር ከመመለሱ በላይ፣ በየደረጃው ያለውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፤ መንግስት የውሃ ሽፋን አነስተኛ ለሆነባቸው አካባቢዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት፣ በፕሮጀክቶች ታግዞ መስራት እንደሚገባ በጽኑ ያምናል፤ በተለይም የለውጡ መንግስት ለቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች በሰራው ስራ የውኃ ተደራሽነት በእጅጉ ማደጉን አንስተዋል። ልምድ ልውውጥ እና ተሞክሮ -ለምክር ቤቶች ሌላው ቅኝታችን በዚህ በተጠናቀቀው ሳምንት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤትና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ መካሄዱን የዳሰሰ ነው። የጋራ የምክክር መድረኩ ዓለማ የልምድ ልውውጥና የልማት ሥራዎችን በመመልከት ተሞክሮ መለዋወጫ ነው።የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ፤ መንግስት ሕዝቡ የሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የምክር ቤቶችን አደረጃጀት ማጠናከርና የክልሉ ሕገ መንግስት ያስቀመጣቸውን ኃላፊነቶች መፈጸም ይገባል ብለዋል።የመንግስት የልማት ኢኒሼቲቮች የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል የሚያስችሉ በመሆናቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መተግበር እንዲችሉ ምክር ቤቶች ያለሰለሰ ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተመልክቷል። የጤና ልማት ስራ እስከ አክሞ ማዳን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ በሚደረግ ጥረት የአጋር ድርጅቶች አስተዋጾ ትልቅ ድርሻ እንዳለውም የተመለከተው በዚህ ሳምንት ነው። ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጋር በመሆን በአርባ ምንጭ ከተማ ያስገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ መሰል የጤና ዘርፍ የልማት ስራዎች መንግስት በዘርፉ የያዘውን ውጥን ከማሳካት አንጻር እገዛቸው ትልቅ መሆኑን አንስተዋል።ማዕከሉ ማህበረሰቡ በቅርበት ሕክምና እንዲያገኝ ከማስቻል ባለፈ ወደ ሌላ አካባቢ ሄዶ ሲታከም ሊያወጣ የሚችለውን ወጪ ያስቀራል። ማዕከሉ የኩላሊት እጥበት ማሽኖች፣ የመድሃኒት ቤት፣ መኝታ አልጋዎችና የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሟልቶ የተገነባ መሆኑም ታውቋል። የከተሞች ኮሪደር- ከቱሪዝም እስክ ኮንፍረንስ ማዕከልነት በኮሪደር ልማት እጅግ ከተዋቡ እና ከደመቁ የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል ሀዋሳ አንዷ ናት። በሳምንቱ የከተማዋ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ማጠናቀቂያ የምስጋናና ዕውቅና እንዲሁም የአራተኛ ዙር የኮሪደር ልማትና የሐይቅ ዳርቻ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄዷል፡፡ የሲዳማ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርቡ ቀጥሏል ብለዋል። በቀጣይ ለሚከናወነው የኮሪደር እና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ስራዎች እንደሚቀጥሉ አንስተው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጎላ መሆኑን ገልፀዋል። የከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነት ለማጠናከር ሥራዎች በላቀ ፍጥነትና ጥራት መከናወናቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ምርጫ -የዴሞክራሲ መሰረት ሳምንቱ በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ከመጠናቀቁ በፊት መራጮች የምርጫ ካርድ ወስደው ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹበትም ነበር። ኢትዮጵያዊያን መጪውን ጊዜ የተሻለ የሚያደርግላቸውን መንግስት ለመመረጥ ዝግጅታቸውን በተግባር እያረጋገጡ ነው።
ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር
Apr 23, 2026 309
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ መጀመሯን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል። ጋዜጠኛ ዳንኤል ኦሊቫሬስ ጋሌጎ በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ እንደገለጸው፣ ይህ ሜጋ ፕሮጀክት አፍሪካውያን ተጓዦች ከአህጉሩ ውጭ ባሉ እንደ ዱባይ፣ ፓሪስና ለንደን ባሉ ማዕከላት በኩል የሚያደርጉትን አድካሚ ጉዞ በማስቀረት፣ አዲስ አበባን የአህጉሪቱ ቀዳሚ የመገናኛ ማዕከል ለማድረግ ያለመ ነው። ከአዲስ አበባ ከተማ በስተደቡብ ምስራቅ 48 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ግንባታ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ተብሎ መጠቀሱን ጋዜጠኛው በዚሁ ጽሁፉ አመልክቷል።   ስራው በይፋ የተጀመረው ባለፈው ጥር ወር ሲሆን፣ አውሮፕላን ማረፊያው በ2023 ዓ.ም (2030 እ.ኤ.አ) የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር፣ በዓመት 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም እንደሚኖረው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ተመልክቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ፣ ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። ይህም አውሮፕላን ማረፊያውን በዓለም ላይ በርካታ ተጓዦችን ከሚያስተናግደው የአትላንታው ሀርትስፊልድ-ጃክሰን አውሮፕላን ማረፊያ ካለው አቅም በላይ እንደሚያደርገው ዳንኤል ኦሊቫሬስ ጋሌጎ ባሰፈረው ጽሁፍ አብራርቷል። አውሮፕላን ማረፊያው ከመንገደኞች አገልግሎት ባለፈ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠናን (AfCFTA) በላቀ ሁኔታ ለመደገፍ ታቅዶ የተገነባ መሆኑን ጋዜጠኛው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ በዝርዝር አስቀምጧል።   በዓመት 3 ነጥብ 73 ሚሊዮን ቶን ጭነት የማስተናገድ አቅም ያለው ይህ መሠረተ ልማት፣ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የአፍሪካን የጭነት በረራ ፍላጎት በሚገባ ምላሽ መስጠት የሚችል መሆኑን ተጠቁሟል። የአውሮፕላን ማረፊያው የተርሚናል ዲዛይን በዓለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ በሆነው ዛሃ ሃዲድ አርክቴክትስ የቀረበ መሆኑን የጠቀሰው ጋዜጠኛው፣ዲዛይኑ የኢትዮጵያን ታላቁ ስምጥ ሸለቆና የተለያየ መልክዓ ምድራዊ ውበትን የሚያንፀባርቅ መሆኑን በጽሁፉ አካቷል። ተጓዦች በአውሮፕላን ማረፊያው ውስጥ ሲዘዋወሩ የኢትዮጵያን ባህልና ተፈጥሮ እንዲመለከቱ በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፣ለዘላቂነት ቅድሚያ በመስጠት የፀሐይ ብርሃን ኃይልንና የዝናብ ውሃ አሰባሰብ ስርዓትን እንዲጠቀም ተደርጎ ተቀርጿል።   በአጠቃላይ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጠናቀቅ፣ኢትዮጵያ በአፍሪካ አቪዬሽን ያላትን መሪነት ከማረጋገጡ ባለፈ የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ትስስር ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ጋዜጠኛው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ደምድሟል። ይህ ፕሮጀክት ከሌሎች የአፍሪካ አየር መንገዶች ጋር በመተባበር የነጠላ የአፍሪካ አየር ትራንስፖርት ገበያን (SAATM) ወደ ተግባር ለመቀየር የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እንደሚያግዝም ተመልክቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 19, 2026 380
የምግብ ሉዓላዊነት - ከተረጂነት መላቀቂያው መንገድ በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ ከተረጂነትና ጠባቂነት መፋቻ መንገዶች መካከል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አንዱ ብልኀት አድርጋ እየታተረች ነው። ይህን ተከትሎም የዜጎችን የምግብ ፍላጎት በራስ የምርት ዐቅም የመሸፈን ሥራ በመከወን ከጠባቂነት ለመላቀቅ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ስኬታማ ናቸው። ለዚህም ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ከልመና ወጥታ ወደ ውጭ ገበያ መላክ መጀመሯ አሥረጅ ነው። በመሆኑም ከውጭ የኢኮኖሚ ጥገኝነት በመላቀቅ የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት ለማስከበር በስንዴ ልማት የተመዘገበውን ስኬት በሌሎች የግብርና ዘርፎች ለመድገም ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም መሠረት በሩዝ፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ሻይ ቅጠል እና ሌሎች የተለያዩ ሰብሎች ላይ እየተከናወነ ያለው ሥራ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው። የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የግብርና ድርጅት (ፋኦ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምግብ ዋስትናና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ የአመራር ቁርጠኝነት የአግሪኮላ ሜዳሊያ በ2016 ዓ.ም ማበርከቱ ለምግብ ሉዓላዊነት ጥረት የተሰጠ ዕውቅና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ረሃብን ከማስቀረት ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ብሔራዊ ብልጽግናን ዕውን ለማድረግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሃብቶች፣ተስማሚ የዓየር ንብረት፣ ለሥራ ትጉ የሆነ ወጣት እንዳላት እና እነዚህን ሃብቶች ታሳቢ በማድረግ የታሪክ ዐውራ የሆነችውን ሀገር ልማት ወደፊት ለማራመድ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ እንደከፈልን ሁሉ፤ ከምግብ ጥገኝነት ለመላቀቅ በትጋት መሥራት ይገባል ሲሉ ማስገንዘባቸው ይታወሳል። የምግብ ሉዓላዊነት፣የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት፣ የበጀት ሉዓላዊነት ታላቁን የሀገር ሉዓላዊነት በጽናት የሚያቆሙ መሆናቸውንም አብራርተዋል። እነዚህን የሉዓላዊነት ዘርፎች ለማስከበርም ብሔራዊ ዐርበኝነት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። ሀገራዊ ትልሙ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት የሚያሸጋግር መልካም ጅማሮ ነው።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 19, 2026 253
ክልሎች፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የንፋስ ሃይል በቀጥታ የምናመራው በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ ነው። በኢተያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው የመረቁትን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን እንመለከታለን። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 100 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል ልማት ወደ ፊት እየተራመደች መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ሥራ ነው። ኢትዮጵያ ዘንድሮ ከጉባ እስከ አሰላ፣ ገናሌ እና አይሻ በሃይል ልማት ዘርፍ ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ፕሮጀክቶች አስመርቃለች። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ደግሞ በዚህ ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀምሯል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩም በምርቃቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ከለውጡ በፊት የነበረው 4 ሺህ ሜጋ ዋት የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በመድረስ ከእጥፍ በላይ እድገት የተመዘገበበትን ትልቅ ስኬት አንስተዋል። የስንዴና ገብስ ሰብሎችን በከፍተኛ መጠን የሚያመርተው አርሲና አካባቢው አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ሃይል የሚመረትበት አካባቢ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እናስቀጥላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። ቢሾፍቱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማም በዚህ ሳምንት በቢሾፍቱ ሀርሰዴ አዳራሽ መካሄዱ ይታወቃል። በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ስኬታማ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይም የክልሉን ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ የከተማ እና የገጠር የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ነው ያስረዱት።   ከዚህ ባለፈ የክልሉን የልማት ሥራዎች ለማቀላጠፍ የሚያግዙ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የአገልግሎት አሰጣጥ አሰራሮች መተግበራቸውንም ተናግረዋል። የቢሾፍቱ መድረክ በድምሩ የግብርና፣ የገጠርና የከተሞች ልማት፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ክንውን በዝርዝር የታየበት ውጤታማ መድረክ እንደነበረም ተመላክቷል። የአሎማ ክላስተር ሌላ የሳምንቱ ዓበይት ጉዳይ ወደ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ይወስደናል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በይፋ አገልግሎት መስጠት የጀመረው በዚህ ሳምንት ነው። በመስኖ የለማ የስንዴ ክላስተር የተጎበኘበትና በተሁለደሬ ወረዳ በክላስተር ለሚከናወነው የተቀናጀ የፍራፍሬ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ የተጀመረበት እንዲሁም የክልሉ የ10 ዓመት የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገበትን ሁነት እናገኛለን።   በእነዚህ ሁነቶች ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የመደመር መንግሥት በሁሉም ዘርፎች ለሀገር እድገትና ማንሰራራት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም በግብርና፣ በመስኖ ልማት፣ በቱሪዝምና ሌሎች መስኮች በተግባር የተመለከትናቸው የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። የአሎማ ክላስተር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የሓይቅ ዳር አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የማቻል ጥረት በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን የሚያሳዩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሀገርን የማሻገር ሥራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የታሪክ መሰነጃ የሳምንቱ በረራችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ የሰው ልጅ መገኛ፣ የኤርታሌ ትኩሳት የሚገነፍልባትና የአዋሽ ወንዝ የተንጣለለባት አፋር ክልል ገብተናል። በአፋር ቆይታችን ትኩረታችንን ሰመራ በማድረግ በስፍራው ሊገነባ የታሰበውን የሉሲ ሙዚየም እንመለከታለን። ሙዚየሙን ለመገንባት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እና የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ የፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት አድርገዋል። ለሉሲ አፋር ቤቷ ነው፤ ሀዳር የተባለው ስፍራ ደግሞ መገኛዋ ነው። በመሆኑም በዚህ ከሰው ልጅ መገኛ ጋር የተቆራኘን ስፍራ ሙዚየም ገንብቶ፣ የቱሪስት መስህብ አልምቶና አካባቢውን በስፋት አስተዋውቆ የገቢ ምንጭ ማድረግ ሲቻል ለምን ተዘንግቶ ቆየ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ይሆናል። የጊዜ ጉዳይ ሆኖ አሁን አፋር ሰመራ ላይ በሉሲ የተሰየመ የሀገር ታሪክና ቅርስ ማጣቀሻ፤ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ማሳያ የሆነ ሙዚየም ለመገንባት ዝግጅት መደረጉ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል።   የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር)፤ የሚገነባው ሙዚየም የሀገር ታሪክና ቅርስ የሚሰነድበት፣ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ተጠብቀው የሚዘልቁበት፣ የሰው ልጅ አመጣጥና ዝግመተ ለውጥ የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ የሚካሄድበት ይሆናል ብለዋል። እሳቸው እንዳሉት የሙዚየሙ ግንባታ በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገለግሎት የሚበቃ ይሆናል። የአፋር ክልል በመስኖ ቢያለሙበት፣ የጥጥ እና የቴምር ልማት ቢካሄድበት ተዝቆ የማያልቅ እምቅ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በለውጡ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን እምቅ የቱሪዝም ሃብቱንም በማልማትና በመጠበቅ የሃገር ሃብት የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የሉሲ ሙዚየም ግንባታ ሁነኛ ማሳያ ነው። የሳምንቱ ቅኝታችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ በቀጥታ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝተናል። አሶሳ በሳምንቱ በሃይማኖት አባቶች ጸሎትና ዱአ ተባርካ ስለ ሰላምና አብሮነት የሚመከርባት ከተማ ሆና እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። የተለያዩ የኃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት 7ኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ "ሰላምን ይበልጥ ለማስፋት እና ለማስረጽ የሃይማኖቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ አባቶች ስለ ሰላም እና አብሮነት እንትጋ ለትውልድ ግንባታም መስራት ግድ ይለናል በማለት አፅንኦት በመስጠት መክረዋል።   የኢትዮጵያ ሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኃይማኖቶች ለሰላም እና ለህዝቦች አብሮነት ያላቸውን አስተምህሮ በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ እና ሀገራዊ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን አለባቸው ብለዋል። በኢትዮጵያ ሰላምን ለማጽናት እና የወንድማማችነት ድልድይን ለመገንባት እንስራ በማለትም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ስንጓዝ የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ-AGRA) ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የኤልቶ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ዩኒየን የሥራ እንቅስቃሴን መጎብኘታቸውን እናገኛለን። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጥምረቱ የቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ አርሶ አደሮች ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ጥሩ ተስፋ የተሰነቀበት መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። የግብርና ልማትን የማዘመን፣ ምርታማነትን የማሳደግና የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል።   የጥምረቱ ፕሬዚዳንት አሊስ ሩህዌዛ፤ በአፍሪካ የግብርና ስርዓት ሽግግርን ለማጠናከር በተለይም አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። በአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ሂደት ውስጥ ደግሞ የኢትዮጵያ ለውጥ አስደናቂ ስለመሆኑ አንስተዋል። ሌሎች በዚህ ሳምንት በሁሉም ክልሎች ባደረግነው ምልክታ በተለይም የምርጫ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኖ ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን እየወሰዱ ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎችም የምረጡኝ ቅስቃሳ ማድርጋቸውን ቀጥለዋል። የግብርና ልማት ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እና ሌሎችም የልማት ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ የቀጠሉበት ሳምንት ነበር ማለት ይቻላል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 253
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። ‎አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። ‎በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ‎የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (‎5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (‎ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ‎‎ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። ‎‎የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ጤና ከሀገር በቀል ስኬት ወደ አህጉራዊ መሪነት
Apr 23, 2026 289
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ እያከናወነች ያለችው ስራ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂካዊ የሆኑ ተቋማዊና የፖሊሲ መሰረቶች ተጥለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መቋቋም ለሀገራዊ ችግሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ መፍትሄ ለማግኘት ትልቅ አቅም የፈጠረ ሲሆን፣ ብሄራዊ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ ተቀርጾ መጽደቁ ደግሞ የዘርፉን ልማትና አጠቃቀም በተደራጀ መንገድ ለመምራት አስችሏል። እነዚህ እርምጃዎች ሀገሪቱ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እና 2030 ስትራቴጂ ውስጥ ቴክኖሎጂውን እንደ ቁልፍ የለውጥ አቅጣጫ እንድትጠቀም በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ዘላቂ ለማድረግም በሰው ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በኮዲንግ፣ በዳታ ሳይንስ እና በክህሎት ለማሰልጠን የተጀመረው ግዙፍ ፕሮግራም የለውጡ አንቀሳቃሽ ኃይል እየሆነ ነው። ከዚህም ባለፈ፣ በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ እንዲገነባ መታቀዱና በዚህ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባልነት ውስጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት እንዲሳተፍ መወሰኑ፣ ሀገሪቱ ቴክኖሎጂውን ለውሳኔ ጥራትና ለምርምር በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀመችበት መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ እንደገለጸው፣ ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በሹመት ደብዳቤው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ AI ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አክሎ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የAI አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል እና በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ለሀገራዊ ለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ በዝርዝር አስፍሯል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የAI ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የተያዘው ሥራ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክርም ተገልጿል። ይህ አህጉራዊ እውቅና በተለይ በጤናው ዘርፍ የታዩ ውጤቶችን ያካትታል። ኢትዮጵያ በኤአይ የታገዘ ዲጂታል ኤክስሬይን ለሳንባ ነቀርሳ ምርመራ ካዋሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። በተጨማሪም የ"HEP Assist" መተግበሪያን በሙከራ ደረጃ በማስጀመር፣ በገጠር የሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ውስብስብ ምልክቶችን ሲያዩ ሙያዊ የሕክምና ውሳኔ እንዲሰጡ ድጋፍ እየተደረገ ነው። እነዚህ የዲጂታል ጤና ስራዎች በ7 ክልሎችና በ15 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ መጀመራቸው፣ ቴክኖሎጂው በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የአገልግሎት ልዩነት ለማጥበብ ያለውን ፋይዳ ያሳያል።   በአጠቃላይ፣ የኤአይ ቴክኖሎጂ በጤናው ዘርፍ ከሚሰጠው የጡት ካንሰር፣ የአንጎል እብጠትና የቆዳ በሽታዎች ምርመራ ባለፈ፣ በግብርና፣ በፋይናንስና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥም በስፋት እየገባ ይገኛል። በ2030 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ሆስፒታሎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል አገልግሎት ለመቀየር የተቀመጠው ግብ፣ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የጀመረችውን የቴክኖሎጂ ነጻነትና የመሪነት ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓት በጤና፣ በግብርና እና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በጤናው ዘርፍ እንደ ካንሰር እና ሳንባ ነቀርሳ ያሉ በሽታዎችን ቀድሞ በመለየት የህክምና ጥራትን ሲያሻሽል፣ በግብርናው ደግሞ የሰብል ተባዮችንና የቡና በሽታዎችን በመለየት ምርታማነትን እያሳደገ ነው። ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂው በመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ እና በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ሰፊ የመረጃ ትንታኔዎችን በፍጥነት በማከናወን፣ የሥራ ፍጥነትን እና የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል። የዘርፉ ፋይዳ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባለፈ የሀገሪቱን የዲጂታል ሉዓላዊነት እና የሰው ኃይል አቅም በመገንባት ላይ ያተኩራል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶችን በኮዲንግ እና በዳታ ሳይንስ በማሰልጠን እንዲሁም የፈጠራ ማዕከላትን (Startups) በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በሌሎች ላይ ጥገኛ ከመሆን ወጥታ የራሷን የዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ይህም በአህጉር ደረጃ ለሚደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች እንደ አርአያ በመሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ ፍትሃዊነት የመጠቀም ጥቅል ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አድርጎታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሹመት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ ያጎላል። በተጨማሪም ሹመቱ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና አፍሪካ በኃላፊነትና በፍትሐዊነት በታጀበ የኤአይ አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንድትሆን የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣም ያደርጋታል።
ኢትዮጵያ በአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ መንገድ
Apr 21, 2026 1521
(በዮሐንስ ደርበው) ታሪክ እንደሚነግረን፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ዕውቅና ያገኘው የኢንዱስትሪያዊ ንብረት ጥበቃን በሚመለከተው በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1883 በተፈረመው የፓሪስ ስምምነት እንዲሁም፤ በ1886 የተፈረመውን የሥነ-ጽሑፍና ሥነ-ጥበብ ሥራዎች ጥበቃን የተመለከተውን የበርን(ስዊዘርላንድ) ስምምነት ተከትሎ ነው። እነዚህ ስምምነቶችም በዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት የሚተዳደሩ መሆናቸው ይታወቃል። ኢትዮጵያ የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣንን፤ በ2022 ዓ.ም ፈጠራንና ኢኖቬሽንን በማበረታታት የፈጠራ ሐሳቦችን ወደ ዕሴት በመለወጥ ሂደት ለሀገራዊ ብልጽግና ቁልፍ ሚና የሚጫወት በአፍሪካ ተምሳሌት የአዕምሯዊ ንብረት ተቋም ለማድረግ እየታተረች ነው። ለዚህ ርዕይ መሳካትም፤ ተቋሙ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት ለሀገራዊ ፈጠራ መጎልበት፣ የኢኖቬሽን፣ ቴክኖሊጂ ሽግግር እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ማደግ ጥቅም ላይ የሚውልበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ሀገራዊ የመዋቅር ሽግግርን መደገፍ የሚል ተልዕኮ አንግቦ እየሠራ ይገኛል። የእስካሁኑ የንግድ ምልክት፣ ቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና የፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) ምዝገባ   የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ወርቅነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ2015 ዓ.ም እስከ ያዝነው በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ድረስ በንግድ ምልክት፣ በቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና በፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) 20 ሺህ 476 ምዝገባዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ 14 ሺህ 729 የንግድ ምልክቶች፣ 5 ሺህ 254 የቅጅና ተዛማጅ መብቶች እንዲሁም 1 ሺህ 781 የፈጠራ ሥራ ባለቤትነት ምዝገባ በተቋማችን አማካኝነት ተከናውኗል። የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች ምንድን ናቸው? አዕምሯዊ ንብረት ማለት በሰው ልጅ አዕምሮ የሚፈጠሩ የፈጠራ ሥራዎችን የሚመለከት መሆኑን የገለፁት አቶ ብሩክ፤ እነዚህ የፈጠራ ሥራዎች እንደማንኛውም ቁሳዊ ሀብት በንብረትነት የሚታወቁበትን አግባብ የያዘው ሥርዓት ደግሞ የአዕምሯዊ ንብረት መብት እንደሚሰኝ ያስረዳሉ። በዚህ አግባብ፤ የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች እንደማንኛውም ቁሳዊ ንብረት ሁሉ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ባለመብቶች የሚሰጡ የባለቤትነት መብቶች መሆናቸውን እንረዳለን። ለዚህም እንደ ምክንያት የሚቀርበው እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ ወጥ ሥራዎችን ለማመንጨት የፈጠራ ባለመብቶች ዕውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውንና ጊዜያቸውን መስዋዕት በማድረግ ከብዙ ድካም በኋላ ያገኟቸው የፈጠራ ውጤቶች በመሆናቸው ነው። ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ ለምን አስፈለገ? አንድም፤ የሰው ልጅ ቀጣይ ዕድገትና የኑሮ ደኅንነት ዋስትና መሠረት የሚያርፈው በቴክኖሎጂና ባሕል ዘርፎች በሚያሳርፋቸው ፈጠራዊ ብቃቶቹ በመሆኑ እንዲሁም የምርምርና የፈጠራ ሥራዎችን ለማካሄድ ተጨማሪ ሀብት የሚያስገኝ በመሆኑና ይህም የኢኖቬሽን ሥርዓቱን ስለሚያሳድግ ነው ይላሉ አቶ ብሩክ። እንዲሁም፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃና ዘርፉን ለሕዝብ የማስተዋወቅ ተግባር ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማረጋገጥ የድርሻውን ስለሚወጣና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት በአጠቃላይ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ በተሻለ ደረጃ ላይ እንዲቆም ስለሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም፤ ሀገራት ጠንካራ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠሩ ቁጥር ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ የልማት መሣሪያ መሆኑን ይገነዘባሉ። ጠንካራና ፍትሐዊ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠራ ባለቤቶችና በተጠቃሚው ሕዝብ ዘንድ ሚዛናዊ ነው ያሉት አቶ ብሩክ። በአጠቃላይ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን በአጽነዖት አንስተዋል። ዜጎች በአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት እንዴት ተጠቃሚ ይሆናሉ? ባለብዙ ቢሊየን ዶላር የፊልምና ድምጽ ሪከርድስ አሳታሚዎችና ሶፍትዌር ኢንዱስትሪዎች ለብዙ ሚሊየኖች የመዝናኛ ሥራዎች የሚያበረክቱት የቅጅ መብት ጥበቃ በመኖሩ መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አቶ ብሩክ ይናገራሉ። በሌላ በኩል ተጠቃሚዎች የሚፈልጓቸውን ምርቶችና አገልግሎቶችን መለየት የሚያስችላቸው ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ የንግድ ምልክቶች ጥበቃና የመብት ማስከበር ሥርዓቶች ባይኖሩ ኖሮ ተመሳስለው በሚቀርቡ ምርቶችና አገልግሎቶች መታለልና ሌሎችም ችግሮች ያጋጥማቸው እንደነበርም ጠቁመዋል። ስለዚህ ምርቶችን በመሸመት ሂደትም በምርቶችና አገልግሎቶች ላይ ያለምንም ግራ መጋባት ግብይቱን ማከናወን እንደሚያስችላቸው መገንዘብ ይቻላል። እንደ አቶ ብሩክ ገለጻ፤ ለፓተንት የፈጠራ ሥራዎች ጥበቃ በመደረጉ መሰጠት የሚገባቸው ማበረታቻዎች የማይሰጡ ከሆነ፤ የፈጠራ ባለሙያዎች ቀጣይ የምርምር ሥራዎችን ማሳደግና ማስፋት እንደማይችሉ ይገመታል። በቀጣይነት የሚገኙ የተሻሻሉ የፈጠራ ሥራዎች አለመኖራቸው ደግሞ፤ በምርቶች ተጠቃሚና አጠቃላይ የኑሮ መሻሻል ሂደት ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተፅዕኖ ይኖረዋል። የአዕምሯዊ ንብረት ዓይነቶች እንዴት ይመደባሉ? የአዕምሯዊ ንብረት፤ የኢንዱስትሪያዊ ንብረት (Industrial Property) እና የቅጅና ተዛማጅ መብቶች (Copyright and Related Rights) በሚሉ ሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚመደብ ያስረዳሉ። አክለውም፤ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት በውስጡ፤ የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ የኢንዱስትሪያዊ ንድፍ እና የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች የተሰኙ አራት ክፍሎችን እንደሚይዝ ያብራራሉ። ፓተንት ምንድን ነው?፡- ፓተንት ማለት በአንድ ቴክኒካዊ ባሕርይ ባለው የፈጠራ ሥራ ላይ የሚኖር የፈጠራ ባለቤትነት ብቸኛ መብት መሆኑን አቶ ብሩክ አስረድተዋል። የፓተንት መብት በአንድ ምርት (ለምሳሌ ማሽን ወይም የአመራረት ሂደት (Process) ሊሰጥ የሚችል ሲሆን፤ ፈጠራውም ለአንድ ቴክኒካዊ ችግር መፍትሔ የሚያስገኝ መሆን ይኖርበታል ይላሉ። ከፈጠራ ሥራው አመንጪ ይሁንታ ውጭ ሥራውን ገበያ ላይ ማዋል፣ መጠቀም፣ ማሰራጨት፣ መሸጥ ወዘተ… እንደማይቻልም አክለዋል። ፓተንት ለባለ መብቱ የጥበቃ መብት የሚያስገኝ ሲሆን፤ የጥበቃው ዘመንም በአጠቃላይ እስከ 20 ዓመት ሊደርስ ይችላል። ፓተንት የሚያስገኛቸው ሕጋዊ (የጥበቃ) መብቶች፡- የፈጠራ ሥራውን መጠቀም የሚችሉና የማይችሉ ሰዎችን መወሰን፤ ሦስተኛ ወገኖች ሥራውን እንዲጠቀሙ የመፍቀድ ወይም የፈቃድ ውል ስምምነት የመስጠት እንዲሁም የፈጠራ ሥራውን የመሸጥ (ለአዲስ የፓተንት ባለመብት) የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል ሥራ አስፈጻሚው። የፓተንት ሥራዎች ለምን ያስፈልጋሉ?፡- ይህን ሲያብራሩም፤ ፓተንት ለፈጠራ ባለመብቶች ዕውቅናንና ሽልማቶችን (ማበረታቻዎችን) የሚሰጥ በመሆኑ፣ ፈጠራዎቹ የኢኖቬሽን ሥራዎችን ስለሚያጠናክሩና በዚህም ቀጣይነት ያለው የሰው ልጅ ሕይወት መሻሻልን የሚያረጋግጥ በመሆኑ እና በሌሎችም በጎ አስተዋጽዖዎች ፓተንት በዕጅጉ አስፈላጊ ነው ብለዋል። የንግድ ምልክት ምንድን ነው?፡- የንግድ ምልክት ማለት አንድን ምርት ወይም አገልግሎት ከሌላው ምርትና አገልግሎት እንዲለይ ለማስቻል በንግድ ምልክት ባለቤቶች ለምርታቸውና አገልግሎታቸው መለያ እንዲሆን ጥቅም ላይ የሚውል ልዩ ምልክት መሆኑን ተናግረዋል። የንግድ ምልክት ሸማቹ ሕብረተሰብ የሚፈልገውን ምርትና አገልግሎት በቀላሉ ለይቶ እንዲገዛ ከማስቻሉም በላይ በሚገዛው ምርትና አገልግሎት ጥራት ላይ በመተማመን ፍላጎቱን እንዲያሟላ ያደርጋል። የንግድ ምልክት ለባለመብቱ ምን ጥቅም ያስገኛል?፡- ምርቶቹ (አገልግሎቶቹ) በተጠቃሚዎች እንዲለዩለት ወይም እንዲታወቁለት ያደርጋል፣ ክፍያን መሠረት አድርጎ ሦስተኛ ወገን እንዲጠቀምበት የመፍቀድ፣ የንግድ ምልክቶች በራሳቸው ዋጋ አላቸው (የአዕምሯዊ ንብረት ዋጋ ትመና (IP Valuation) ለምሳሌ በፈረንጆቹ በ2026 የመጀመሪያ ወራት አፕል (Apple) 600 ቢሊየን ዶላር፣ ማይክሮሶፍት (Microsoft) 565 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር፣ ጉግል (Google) 433 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ዋጋ ግምት እንደነበራቸው ተብራርቷል። በተጨማሪም፤ የንግድ ምልክት በሕግ በሚቀመጥ የጊዜ ገደብ መሠረት እየታደሠ ለዘላለም ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል፤ የንግድ ምልክት ባለቤቱን በማስተዋወቅ ዕውቅናና የገንዘብ ትርፍን ያስገኛል፤ የንግድ ምልክት ተገቢ ያልሆኑ የንግድ ውድድሮችን በመግታት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል (ተመሳስለው የሚሠሩና ለገበያ የሚቀርቡ ሥራዎችን (Counterfieited Products) ለመዋጋት ዓይነተኛ መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል፤ የንግድ ምልክት ሰዎች ምርቶቻቸውንና አገልግሎቶቻቸውን ሚዛናዊ በሆነ አግባብ እንዲያቀርቡ በማድረግና በብሔራዊና ዓለም አቀፍ ደረጃ የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት እንዲኖር ምቹ ሁኔታ በመፍጠር አስተዋጽዖው የላቀ ነው ብለዋል። ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ምንድን ነው?፡- ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ በምርቶች ሥነ-ውበት (Esthetics) ላይ ተመስርቶ ቅርጽን፣ መስመሮችን ወይም ቀለምን በመጠቀም ለገበያ የሚቀርቡ ምርቶች የገዥዎችን (ሸማቾችን) ቀልብ ለመሳብ እንዲችሉ በምርቶች ላይ የሚገለጽ የንድፍ ጥበብ ዘርፍ ነው ያሉት አቶ ብሩክ፤ ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች በኢንዱስትሪና ዕደ-ጥበብ ምርቶች ላይ ተዘጋጅተው ሊወጡና ለገበያ ሊቀርቡ ይችላሉ ይላሉ። ዘርፉ ከቴክኒካልና ሕክምና መሣሪያዎች አንስቶ እንደ ሠዓት፣ ጌጣጌጦችና ሌሎች የቅንጦት ምርቶች ዕቃዎችን ሊያካትት ይችላልም ብለዋል። የቤት ዕቃዎችን፣ የኤሌክትሪክ መሣሪያዎችን፣ ተሽከርካሪዎችና የሕንጻ ንድፎችን እንዲሁም የጨርቃጨርቅ ንድፍ ውጤቶች በኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ሥር የሚወድቁ ይሆናሉ ይላሉ። ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች ጥበቃ የሚደረግላቸው አዲስ ወይም ወጥ ከሆኑ ብቻ መሆኑን ገልጸው፤ በዲዛይኑ ውስጥ ከሚገለጸው ምርት ጋር ተያያዥ የሆኑ የቴክኒክ ጉዳዮች ጥበቃ እንደማይደረግላቸው አስታውቀዋል። ለኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ጥበቃ ማድረግ ለምን ያስፈልጋል?፡- በምርቶች ውበት ላይ የሚገለጽ በመሆኑ የተጠቃሚውን ዐይን ይስባል፣ የምርቶችን ዋጋ ይጨምራል፣ ፈጠራንና ውድድርን ያበረታታል፣ ለባለመብቱ ብቸኛ መብትን ያጎናጽፋል፣ በኢንዱስትሪዎች፣ ባሕላዊ ጥበብና በዕደ ጥበብ ዘርፍ ፈጠራ በማሻሻል ኢኮኖሚ እንዲያድግ ያደርጋል፣ የወጭ ንግድን (Export Trade) ያሳድጋል በማለት የኢንዱስትሪ ንድፍ ጥበቃ አስፈላጊነትን ያብራራሉ። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካች ምንድን ነው?፡- የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች በምርቶች ላይ የሚቀርቡ ምልክቶች ሆነው እነዚህ ምልክቶች አንድ የተወሰነ አካባቢን በምርቱ ምንጭነት የሚያመላክቱና ጥራትንና ዝናን ከቦታው ጋር አስተሳስረው የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን አቶ ብሩክ ያስረዳሉ። በአብዛኛው የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች ልዩ ምርቱ የሚገኝበትን የቦታ ስም (Specific Local Geographyical Factors – Climate, Soil) ይይዛሉ። ለምሳሌ፡- Roquefort for Cheese -France፣ የማረቆ በርበሬ፣ የሸኖ ቅቤ፣ የዓድኣ ጤፍ … የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሾች ናቸው። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾችን መጠበቅ ለምን ያስፈልጋል?፡- ተጠቃሚዎች ምርቶች የሚገኙበትን ሀገር ወይም አካባቢ በቀላሉ ለመለየት፣ ሕጋዊነት በሌላቸው ወገኖች የምርቱ መገኛ አካባቢ እና የምርቱ ዝና በተሳሳተ መልኩ ለሌላ ምርት መጠሪያ እንዳይውል ለመከላከል ይረዳል ይላሉ። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምንድን ናቸው?፡- የቅጅ መብት በሥነ-ጽሑፍ እና ሥነ-ጥበብ ዘርፍ ወጥ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ደራስያን፣ አርቲስቶች ወዘተ… የባለቤትነት መብት የሚሰጥ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑንም ነው ሥራ አስፈጻሚው የሚያስረዱት። በአንጻሩ ተዛማጅ የቅጅ መብት ማለት ይላሉ አቶ ብሩክ፤ በወጥ የፈጠራ ሥራዎች ላይ ተመስርተው የሚሠሩ ተዛማጅ (Related) የፈጠራ ሥራዎችን ያካትታል። ለምሳሌ፡- ከዋኞቹ (ተዋንያን እና ዘፋኞች)፣ ድምጽ ሪከርዲንግስ፣ አሳታሚዎች (ኮምፓክት ዲስኮች)፣ የብሮድካስት ተቋማት፣ (ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን) የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ዘርዝረዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምን ዓይነት መብቶች ያስገኛሉ?፡- ባለመብቶች ሥራዎቻቸውን ለመጠቀም ወይም ሦስተኛ ወገኖች እንዲጠቀሙባቸው የመፍቀድ፣ ሥራዎች እንዲባዙ፣ ለሕዝብ እንዲዳረሱ፣ እንዲሠራጩ፣ እንዲተረጎሙ ወይም ወደሌላ ሥራ እንዲቀየሩ የመፍቀድ ወይም የመከልከል፣ የደራሲነት (የአመንጭነት) መብት ዕውቅና እንዲያገኙ፣ በብዕር ስም የመጠቀም መብት፣ ክብሩንና መልካም ስሙን የሚያጎድፍ የሥራ መዛባት እንዳይኖር የመጠበቅ ወይም የሥራው ወደሌላ መቀየር የሚያስከትለውን ጉዳት የመቃወም ወዘተ መብቶችን ያስገኛሉ ብለዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ምን ጥቅሞች ያስገኛል?፡- የሰውን ልጅ የፈጠራና ኢኖቬሽን ጥረቶችን ያሳድጋል፣ ለፈጠራ አመንጭዎች መበረታታትን ይፈጥራል፣ የሕጋዊ ተፈጻሚነትን በማረጋገጥ አመንጭዎችና በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች መዋዕለ-ነዋይ እንዲያፈሱ የፈጠራ ሥራዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚኖራቸውን የሥርጭት ሽፋን ያሳድጋል ነው ያሉት አቶ ብሩክ። የፓሪስ ስምምነት አባል ኢትዮጵያ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር ለመሆን ለዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት (WIPO) ያስገባችው ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስምምነቱን ነሐሴ 9 ቀን 2017 ዓ.ም በማጽደቁ ከዚሁ ዕለት ጀምሮ ለስምምነቱ ተገዢ ሆናለች። አቶ ብሩክ እንዳብራሩት፤ የፓሪስ ስምምነት በጥቅሉ የኢንዱስትሪያዊ ንብረቶችን ጥበቃ የሚመለከት ነው። የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ፣ የግልጋሎት ሞዴል (በአንዳንድ ሀገራት ሕግ ኢትዮጵያን ጨምሮ “የአነስተኛ ፈጠራ የባለቤትነት መብት” በመባል የተደነገገ)፣ የአገልግሎት ምልክት፣ የንግድ ስም (የኢንዱስትሪ ወይም የንግድ እንቅስቃሴ የሚካሄድባቸው ስያሜዎች)፣ ጂኦግራፊያዊ አመላካች እና ፍትሐዊ ያልሆነ ውድድርን መከላከል ያካተተ ነው። የስምምነቱ መሠረታዊ ድንጋጌዎች በሦስት ዋና ዋና መርሆዎች እንደሚከፈሉ ጠቁመው፤ እነሱም፡- የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር መሆን በሌሎች አባል ሀገራት ውስጥ እንደ ዜጋ የመስተናገድ መብት፣ የቀዳሚነት መብት የማግኘት፣ በቀላሉ ዓለም አቀፍ ጥበቃ የማግኘት አሠራር እና መሰል ጉልህ ጥቅሞችን የማግኘት ዕድል ይሰጣል ሲሉ ይገልጻሉ። በመሠረቱ የፓሪስ ስምምነት የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃን በማቀላጠፍ አዳዲስ ግኝቶችንና ፈጠራዎችን እንዲሁም የንግድ ሥራዎች ድንበር ሳይገድባቸው የፓተንትና የንግድ ምልክት መብቶች በቀላሉ እንዲጠበቁ በማድረግ ፈጠራን፣ ንግድን እና ኢኮኖሚያዊ እድገትን እውን ያደርጋል ብለዋል። የዘንድሮው የአዕምሯዊ ንብረት ቀን የፊታችን ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም “አዕምሯዊ ንብረትና ስፖርት፤ እንዘጋጅ፣ እንጀምር፣ እንፍጠር!” በሚል መሪ ሐሳብ ዓለም አቀፉ የአዕምሯዊ ንብረት ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል። በስፖርት ዓለም ውስጥ የሚከሰቱ ተወዳዳሪዎች የግልና የጋራ ፈጠራዎች፣ ንድፎች፣ ብራንዶችና የመልካም ዝና ታሪኮችን ለመጠበቅና ሀገራትን ጭምር ለማስተዋወቅ የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃ ሥርዓት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል። ምክንያቱም ስፖርት በባሕርይው በውድድር ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን፤ ከሀገራት ዝና፣ ከፋሽን ዲዛይን፣ ከመዝናኛ፣ ከሚዲያ ሥርጭት፣ ከጤናና ከዕለት ተዕለት መገልገያ ቁሶች ጋር የሚገናኝ በመሆኑ ነው።  
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 1010
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ ‎በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ‎ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3972
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2732
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8515
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 7004
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60994
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 55024
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35517
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33114
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 28058
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27349
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26841
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26364
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60994
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 55024
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35517
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33114
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 284
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው።   በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል።   የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል።   የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል።   ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 612
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም