ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የመደመር መንግስት የፈጠራቸውን መልካም እድሎች በመጠቀም ብልሹ አሰራሮችን መዋጋት ይገባል
Aug 14, 2026 14
አዳማ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግስት የፈጠራቸውን መልካም እድሎች በመጠቀም ለሀገር ልማት በጋራ መትጋትና ብልሹ አሰራሮችንም መዋጋት ይገባል ሲሉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቴ አለነ ገለጹ። የፌዴራል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓል ማጠቃለያ መድረክ "የፀረ ሙስና ትግል ትናንት ዛሬ እና ነገ በሚል መሪ ሀሳብ" በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቴ አለነ፤ የሙስና ትግል የመጀመሪያ ምዕራፍ መከላከልን፣ ምርመራንና ክስን በአንድ ተቋም በማድረግ ይሰራ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም እንቅስቃሴው ህዝብን የትግሉ ባለቤት ያላደረገ፣ የሙስና መከላከል ስራን የረሳና ለትውልድ የስነ-ምግባር ግንባታ ቦታ የማይሰጥ ነበር ብለዋል። በሁለተኛው ምዕራፍ፣ ከሚሊኒየሙ መባቻ ጀምሮ ለውጡ እስከመጣበት ጊዜ ድረስ የነበረው ወቅት በልማታዊ መንግስት ስም ከፍተኛ ጣልቃገብነት የተካሄደበት እንዲሁም ሙስና በከፍተኛ ሁነታ የተስፋፋበት እንደነበር አንስተዋል። በዚህም ምክንያት የህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ ሜጋ የመንግስት ፕሮጀክቶች በሙስና እና በሌብነት ምክንያት ለከፍተኛ ችግር ተዳርገው እንደነበር አውስተዋል። በሶስተኛው ምዕራፍ፣ ማለትም ከሀገራዊ ለውጡ መባቻ ጀምሮ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ ከሙስና ትግል አኳያ መሰረታዊ ለውጥ መደረጉን ገልጸዋል። በኮሚሽኑ ላይ ከተደረጉት ማሻሻያዎች መካከል ዋነኛው የህግ ሪፎርም መሆኑን አንስተው፤ ሙስናን በአንድ ተቋም ብቻ መታገል ስለማይቻል ሁሉም የመንግስት ተቋማት የትግሉ ባለቤት እንዲሆኑ መደረጉን አብራርተዋል። በሶስቱም የመንግስት አካላት መካከል ጥብቅ የመረጃ ቅብብሎሽ፣ ጠንካራ ትስስር እና ቅንጅት እንዲፈጠር የሚያስችል ለውጥ ተደርጓል ብለዋል። ይህም ስርዓታዊ እና መንግስታዊ ሙስና መሰረት እንዳይኖረውና እንዳይፈጠር ለማድረግ የሚያስችል የሚያበረታታ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የዲጂታላይዜሽንን መልካም እድሎች በመጠቀም አገልግሎቶችን ከሰው ንክኪ ነፃ እና አካታች በሆነ መንገድ ማቅረብ መቻሉ፣ መሰረታዊ የእሳቤ ለውጥ ማምጣቱንና ለፀረ-ሙስና ትግሉ ጠንካራ መሰረት እየጣለ እንደሚገኝ አክለው ገልጸዋል። በእነዚህ አዎንታዊ ለውጦች እና የመደመር እሳቤ በፈጠራቸው አዳዲስ እድሎች በመጠቀም፣ በአሁኑ ወቅት ሙስና ጎልቶ በሚታይባቸው ዘርፎች ላይ ያተኮረ ዘመቻ መጀመሩን ለአብነት አንስተዋል። በመሆኑም የተጀመሩ አዎንታዊ ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል፣ በመጪው ጊዜም ያልተቋረጠና የተቀናጀ የሙስና ትግል ማድረግ እንደሚገባ አቶ እውነቴ አሳስበዋል። የፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ እሸቴ አስፋው በበኩላቸው፣ ባለፉት ዓመታት ኮሚሽኑ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የሚያስችሉ ስትራቴጂዎችን ነድፎ ሲንቀሳቀስ መቆየቱንና በዚህም አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። 25ኛ ዓመታችንን ስናከብርም ጠንካራና ደካማ ጎኖቻችንን ነቅሰን በማውጣት በቀጣይ የተሻለ ሥራ ለመሥራት ዝግጁነታችንን እያረጋገጥን ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ የሙስና እና የብልሹ አሰራር ችግሮችን በመፍታት፣ ተጠያቂነትን በማስፈንና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸውን ተግባራት ለማሳለጥ በሚያስችል ጠንካራ ቁመና ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በተለይም ከሀብት ምዝገባ አንጻር አዎንታዊ ለውጦች መኖራቸውን ያነሱት ምክትል ኮሚሽነሩ፣ ሀብታቸውን ባላስመዘገቡ አካላት ላይ ተጠያቂነትን የማስፈን ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በመድረኩ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶን ጨምሮ ከፌዴራልና ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል የማመንጨት አቅሟን በማሳደግ የቀጣናው የኃይል ማዕከል እየሆነች ነው
Aug 14, 2026 43
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ማመንጨት አቅሟን በማሳደግ የቀጣናው የኃይል ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ የውሃ፣ የፀሐይ፣ የነፋስና የጂኦተርማል ብዝኅ የኃይል ፀጋዎች ልማት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅምን ማጎልበት የሚቻልበት ምኅዳር እየፈጠረ ይገኛል። የታዳሽ ኃይል ልማት እመርታዊ ጉዞም የኤሌክትሪክ ማመንጨትን ከልማት፣ ልማትን ከኢኮኖሚ ዕድገት፣ ኢኮኖሚ ዕድገትን ከቀጣናዊ ትስስር ጋር እያሰናሰለ የሚገኝ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ግብ ነው። ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፣ የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር ዘላቂ ኢኮኖሚ እንድትገነባ እያስቻለ ነው። የታዳሽ ኃይል ምንጮቹን በማቀናጀት የሚካሄደው ልማትም የኢንዱስትሪ፣ የግብርና፣ የከተማ ልማትና የዲጂታል ኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የኃይል መሠረተ ልማት እየገነባ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የውሃ፣ የፀሐይ፣ የነፋስና የጂኦተርማል ሃብቶችን በማልማት የኤሌትክትሪክ የኃይል ምንጮችን፣ ደህንነትና ዘላቂነትን በማጎልበት የኢኮኖሚ መሠረት መፍጠር እየተቻለ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በዜጎች ትብብርና በሀገር አቅም የተገነባው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ የኃይል ልማት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን አስረድተዋል። የሕዳሴ ግድብ የኃይል አቅርቦት አቅም የኢትዮጵያን ፍላጎት ለማሟላት ከማገዙ ባሻገር፣ ኃይልን ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ የቀጣናዊ ኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር አዲስ ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። ይህም ኃይል ለኢትዮጵያ ዕድገትና ልማት የሚውል ግብዓት ብቻ ሳይሆን የንግድ፣ የዲፕሎማሲና የቀጣናዊ ትብብር መሣሪያ እየሆነ መምጣቱን እንደሚያመላክት አብራርተዋል። የዓለም አቀፍ የውሃና የኃይል ገበያ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታን ታሳቢ በማድረግም ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ፀጋዎቿን በማልማት ከሀገር ውስጥ የኃይል ፍላጎት ባሻገር ቀጣናዊ ትስስርን እያሰፋች መሆኗን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት እመርታዊ ጉዞም ኃይልን ከማመንጨት የተሻገረ ቀጣናዊ የጋራ ዕድገትና ብልፅግናን የማፋጠን አህጉራዊ የልማት ግብ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በዚህም ስትራቴጂካዊ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የራሷን የኃይል ደህንነት ከማረጋገጥ ባሻገር ለምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስርና ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ውህደት የሚያግዝ አዲስ ምዕራፍ እየገነባች ነው ብለዋል። ለአብነትም ከጅቡቲ፣ ኬንያና ሌሎች ጎረቤቶች ጋር ያለውን የኃይል ትስስር በማስፋፋት የጋራ ዕድገትና ብልፅግናን የሚያጎለብቱ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። በቀጣይም ደቡብ ሱዳንና ሶማሊያን ጨምሮ ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብና የኃይል ትስስር መሠረተ ልማትን ለማስፋፋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። የኃይል ሽያጩም ኢትዮጵያን የኃይል ማዕከል በማድረግ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ምንጭ በመሆን ጭምር ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጋር ተሰናስሎ መቀጠሉን ተናግረዋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው
Aug 14, 2026 46
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ) ፦ የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ የተቋማት አፈፃፀምን ጨምሮ፣ የሴፍቲኔት፣ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተከናወኑ ተግባራትና ሌሎች ኢኒሼቲቮችን ገምግሟል። የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው። ዛሬ ለአንድ ሰው የዘራነው ተስፋ ነገ ለማኅበረሰባችን የሚያፈራ ፍሬ ይሆናል፣ ዛሬ የረዳነው ወገን ነገ ሌላውን ለመርዳት የሚነሳ ዜጋ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። በጎ ፈቃድ አንድ ጊዜ የሚደረግ ተግባር ሳይሆን ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር የመልካምነት ባህል በመሆኑ ባህሉን በማዳበር ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል። በሌላ በኩል በክልሉ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የቅዳሜ ገበያዎችን ተደራሽ በማድረግ የተጀመሩ ተግባራትን ማጎልበት እንደሚገባ ገልፀዋል። ዜጎችን ከተረጂነትና ከጥገኝነት በማላቀቅ ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙ ምርታማነታቸውን በማሳደግ የተጀመሩ ተግባራትም ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ሁሉም አመራር የበኩሉን ሀላፊነት እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ የመንግስት እና የፓርቲ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በምክክር ጉባኤው እየተነሱ ያሉት ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው
Aug 14, 2026 39
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከተመካካሪዎች እየተነሱ የሚገኙ ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገትና የተሻለ መጻኢ ጊዜ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ተመካካሪ አበራ አኔቦ፤ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደፊት የሚያሻግሩና የጋራ ሀገርን መገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች ከተመካካሪዎች እየተነሱ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው ምክክር ለሀገራችን ዘላቂ ጥቅም የሚያስገኝ እና ለመጪው ትውልድም መልካም አርአያ የሚሆን ታሪካዊ ጉባኤ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ይህም ለኢትዮጵያ ቀጣይነት ላለው ዘላቂ ዕድገት ምቹ ዕድል ይዞ እንደሚመጣ ታላቅ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። ተመካካሪ ወይዘሮ ኦድንጊሊ ሎ፤ አካታች እና አሳታፊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እጅግ አስፈላጊ በሆነ ወቅት መከናወኑን ሂደቱም የተሳካና የኢትዮጵያን የወደፊት ጉዞ የሚያስቀጥሉ መልካም አጋጣሚዎችን መፍጠሩን ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያንን በተወካዮቻቸው በምልዓተ ያሳተፈ መሆኑንና ኢትዮጵያን አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስችሉ ጠቃሚ ሀሳቦች በነጻነት እንዲነሱ ምቹ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሀገሪቱን ብዝሃነት ያንጸባረቀ እና ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ አዎንታዊ የምክክር ጉባኤ እንደሆነም ነው ያነሱት። ሌላኛው ተመካካሪ ታደሰ ዳኜ በበኩላቸው፤ ለሀገር አንድነት ምክክር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝና መልካም ውጤት ይዞ ይመጣል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል። ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች የወከሉ ተመካካሪዎች በነጻነትና አሳታፊ በሆነ መልኩ እየተመካከሩ በመሆኑ ሀገራዊ ምክክሩ ውጤታማ ነው ብለዋል።
የምክክር ጉባኤው የዘመናት ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት ነው-ተመካካሪዎች
Aug 14, 2026 51
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታትና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ የጋራ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በምክክሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች፤ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የጋራ የመፍትሔ ሀሳብ የቀረበበት መሆኑን ተናግረዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ነኢ አለልኝ ምክክሩ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግር ጠቃሚ ግብአቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በሀገሪቱ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮች ላይ በስፋት ተመካክረን የመፍትሔ ሀሳቦችን አስቀምጠናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ኒሽራ ሱሌይማን ሀሳባችንን በነጻነትና በግልጽ በማቅረብ የመፍትሄ ሀሳቦች ላይ ምክክር እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። ምክክሩ መግባባት የሰፈነባት ያደገችና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ምክክሩ ለሀገር የሚበጁ ጠቃሚ ግብዓቶች የተገኙበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ደራራ ጣፋ ናቸው።
ፖለቲካ
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው
Aug 14, 2026 46
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ) ፦ የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ የተቋማት አፈፃፀምን ጨምሮ፣ የሴፍቲኔት፣ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተከናወኑ ተግባራትና ሌሎች ኢኒሼቲቮችን ገምግሟል። የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው። ዛሬ ለአንድ ሰው የዘራነው ተስፋ ነገ ለማኅበረሰባችን የሚያፈራ ፍሬ ይሆናል፣ ዛሬ የረዳነው ወገን ነገ ሌላውን ለመርዳት የሚነሳ ዜጋ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። በጎ ፈቃድ አንድ ጊዜ የሚደረግ ተግባር ሳይሆን ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር የመልካምነት ባህል በመሆኑ ባህሉን በማዳበር ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል። በሌላ በኩል በክልሉ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የቅዳሜ ገበያዎችን ተደራሽ በማድረግ የተጀመሩ ተግባራትን ማጎልበት እንደሚገባ ገልፀዋል። ዜጎችን ከተረጂነትና ከጥገኝነት በማላቀቅ ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙ ምርታማነታቸውን በማሳደግ የተጀመሩ ተግባራትም ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ሁሉም አመራር የበኩሉን ሀላፊነት እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ የመንግስት እና የፓርቲ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በምክክር ጉባኤው እየተነሱ ያሉት ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው
Aug 14, 2026 39
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከተመካካሪዎች እየተነሱ የሚገኙ ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገትና የተሻለ መጻኢ ጊዜ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ተመካካሪ አበራ አኔቦ፤ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደፊት የሚያሻግሩና የጋራ ሀገርን መገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች ከተመካካሪዎች እየተነሱ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው ምክክር ለሀገራችን ዘላቂ ጥቅም የሚያስገኝ እና ለመጪው ትውልድም መልካም አርአያ የሚሆን ታሪካዊ ጉባኤ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ይህም ለኢትዮጵያ ቀጣይነት ላለው ዘላቂ ዕድገት ምቹ ዕድል ይዞ እንደሚመጣ ታላቅ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። ተመካካሪ ወይዘሮ ኦድንጊሊ ሎ፤ አካታች እና አሳታፊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እጅግ አስፈላጊ በሆነ ወቅት መከናወኑን ሂደቱም የተሳካና የኢትዮጵያን የወደፊት ጉዞ የሚያስቀጥሉ መልካም አጋጣሚዎችን መፍጠሩን ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያንን በተወካዮቻቸው በምልዓተ ያሳተፈ መሆኑንና ኢትዮጵያን አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስችሉ ጠቃሚ ሀሳቦች በነጻነት እንዲነሱ ምቹ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሀገሪቱን ብዝሃነት ያንጸባረቀ እና ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ አዎንታዊ የምክክር ጉባኤ እንደሆነም ነው ያነሱት። ሌላኛው ተመካካሪ ታደሰ ዳኜ በበኩላቸው፤ ለሀገር አንድነት ምክክር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝና መልካም ውጤት ይዞ ይመጣል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል። ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች የወከሉ ተመካካሪዎች በነጻነትና አሳታፊ በሆነ መልኩ እየተመካከሩ በመሆኑ ሀገራዊ ምክክሩ ውጤታማ ነው ብለዋል።
የምክክር ጉባኤው የዘመናት ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት ነው-ተመካካሪዎች
Aug 14, 2026 51
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታትና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ የጋራ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በምክክሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች፤ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የጋራ የመፍትሔ ሀሳብ የቀረበበት መሆኑን ተናግረዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ነኢ አለልኝ ምክክሩ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግር ጠቃሚ ግብአቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በሀገሪቱ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮች ላይ በስፋት ተመካክረን የመፍትሔ ሀሳቦችን አስቀምጠናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ኒሽራ ሱሌይማን ሀሳባችንን በነጻነትና በግልጽ በማቅረብ የመፍትሄ ሀሳቦች ላይ ምክክር እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። ምክክሩ መግባባት የሰፈነባት ያደገችና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ምክክሩ ለሀገር የሚበጁ ጠቃሚ ግብዓቶች የተገኙበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ደራራ ጣፋ ናቸው።
የስራ ቡድኖች የአጀንዳ ምክረሃሳቦቻቸውን ለሚያደራጀው ቡድን እያቀረቡ ነው
Aug 14, 2026 67
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የስራ ቡድኖች ሁሉም ቡድኖች ያዘጋጇቸውንና የተስማሙባቸውን ምክረ-ሀሳቦች እንዲያናብብ፣ እንዲያጣጥም እና እንዲያደራጅ ለተቋቋመው እና 120 አባላት ላሉት ቡድን በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡ ይህ ቡድን ከስምንቱ ባለ 500 አባላት የስራ ቡድን በተመረጡ 15 አባላት የተዋቀረ ሲሆን መግባባት የተደረሰባቸውን የሁሉንም አጀንዳዎች ምክረሃሳቦች አዳምጦ የሚያጣጥም፣ በሚቀርቡ ሀሳቦች መካከል መጣረስ እንዳይኖር ጥንቃቄ የሚያደርግና ለጠቅላላ ሀሳቦቹ ወጥነት በመፍጠር 4ሺ አባላት ላሉት ዋናው ጉባኤተኛ አደራጅቶ የሚያቀርብ ነው፡፡ ቡድኑ በአሁኑ ሰዓት ከእያንዳንዱ የስራ ቡድን የመጡ ምክረሃሳቦችን በማዳመጥ ላይ መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያን በሀገራዊ አጀንዳዎቻቸው ላይ በጋራ የሚመክሩበትን ዕድል ፈጥሯል
Aug 13, 2026 296
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያን በሀገራዊ አጀንዳዎቻቸው ላይ በጋራ የሚመክሩበትን ዕድል መፍጠሩን ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያን ለዘመናት ሲፈትኗት የቆዩ ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልዩነቶችና አለመግባባቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በንግግር ለመፍታት የሚያስችል እድል ተፈጥሯል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤም ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር የሚችሉበትን ታሪካዊ ምዕራፍ ከፍቷል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ዋናው ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ ቆይቶ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ተመካካሪ ቄስ ተሻለ አለባቸው ለኢዜአ እንዳሉት፤ ጉባኤው በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በስፋት እየመከረ ነው፡፡ በየደረጃው ያሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች የታደሙበት፣ የሀሳብ ብዝሃነት የሚስተናገድበት አካታችና አሳታፊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምክክሩ ለዘመናት የኢትዮጵያውያን የልዩነት ምንጭ ሆነው የዘለቁ አጀንዳዎችን የያዘ መሆኑን ገልጸው፤ ለሀገር የሚበጁ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩበት ነውም ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተጀመረው ምክክር ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ ለቀጣዩ ትውልድ ተሞክሮ እንደሚወሰድበት ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በዓድዋና በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ የጻፍነውን አኩሪ ታሪክ በምክክሩ ላይ በመድገም ለትውልድ አሻራ አስቀምጠን እናልፋለን ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ተመካካሪ ድንቅነሽ ኡባራ በበኩላቸው፤ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ተመካካሪዎች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ለሀገር ይጠቅማል ያሉትን የየራሳቸውን ሀሳብ ማንጸባረቃቸውን ገልጸው፤ ጉባኤው በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መፍትሔ ማስቀመጥ እንደሚቻል አመላክቷል ብለዋል፡፡ ጉባኤው ዜጎች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር የሀገር ሁለንተናዊ ልማት እንቅፋቶችን በማለፍ ለነገው ትውልድ የተሻለች ሀገር ማስረከብ የሚያስችል ምቹ ምኅዳር መፍጠሩን የገለጹት ደግሞ ተመካካሪ አበራሽ አባይነህ ናቸው፡፡ ተመካካሪዎች መደማመጥን መርህ በማድረግ ለምክክር በተመረጡ አጀንዳዎች ላይ አንድነትን የሚያጠናክሩ ሀሳቦችን መሰንዘራቸውን ገልጸው፤ ሀገርን የሚያጸና መፍትሔ እንደሚመጣ ተስፋ ሰንቄያለሁ ብለዋል፡፡
በ8 የአጀንዳ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲመካከሩ የቆዩት የአጀንዳ ቡድኖች መግባባት ላይ ደረሱ
Aug 13, 2026 300
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ከሁለት ቀናት በፊት በሰላም ግንባታ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በመንግስት አደረጃጀት እና የፖለቲካ ስርዓት ሲመካከሩ የነበሩ ቡድኖ መግባባት ላይ እንደደረሱ መገለፁ የሚታወስ ነው፡፡ በዛሬው ዕለትም የተቀሩት ማለትም በሀገር ግንባታ ፣በፌዴራል ከተሞች ጉዳይ፣ ተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነት እና ሰብዓዊ መብት፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተመካካሪዎች ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
የኢትዮጵያውያን ታሪካዊ የጋራ ውል
Aug 13, 2026 274
በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አሁን ላይ የሕዝቡን የጋራ እይታ ወደሚያንጸባርቁ ተጨባጭ የምክረ-ሃሳብ ሰነድ በመቀየር ላይ ይገኛል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ያለውና ነገ አንድ ወሩን የሚደፍነው ይህ ታሪካዊ ጉባኤ፣ የልዩነቶችን በር እየዘጋ የጋራ ወደሆኑ መፍትሔዎች እየተሸጋገረ ይገኛል። በጉባኤው ላይ ከሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች የተወጣጡ 4ሺህ የሕዝብ ወኪሎች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ፣ ይህም የውይይቱን አሳታፊነትና ህዝባዊ መሰረት በእጅጉ የሚያጎላ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዋናው ጉባኤው የሚሆኑ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ በማድረግ ወደ ውይይት ተገብቷል። እነዚህም አጀንዳዎች የሀገር ግንባታን፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽን፣ የፖለቲካና የምርጫ ሥርዓትን፣ የፌዴራል ከተሞች ጉዳይን፣ የሃይማኖት ጉዳዮችን፣ የተቋማት ግንባታን፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶችን፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን፣ የሙስናና መልካም አስተዳደር ችግሮችን እንዲሁም የሰላም ግንባታን ያካተቱ ናቸው። እያንዳንዱ አጀንዳ በ500 አባላት በተደራጁ ስምንት ልዩ የሥራ ቡድኖች ተከፍሎ ሲመካከርባቸው ቆይቷል። ባለፉት ሳምንታት በተካሄዱት ተከታታይ ውይይቶች ተሳታፊዎች እርስ በእርስ በመደማመጥ፣ ልዩነቶችን በመሰብሰብ እና ወደ አማካይ ሃሳብ በመምጣት በኩል ትልቅ እርምጃ ማሳየት ችለዋል። ተሳታፊዎቹ በመግባባት የተዘጋጁትን የተጠናከሩ ምክረ-ሃሳቦች በመቀበልና የቃለ-ጉባኤ ሰነዶችን በመፈራረም ለወደፊቱ የሀገሪቱ አቅጣጫ መሠረት የሚሆን የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። የሥራ ቡድኖቹ የመጀመሪያ ምዕራፍ ስራቸውን በማጠናቀቃቸው፣ አሁን ሂደቱ ወደ ሁለተኛውና ወሳኙ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተበታተኑትንና በተለያዩ ቡድኖች የቀረቡትን ምክረ-ሃሳቦች ወጥነት ባለው መልኩ ለማደራጀትና ለማጣጣም ስምንት ልዩ ቡድኖች ተዘጋጅተዋል። የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ የሂደቱ አጠቃላይ ሂደት ሦስት አራተኛ ያህል መጠናቀቁ ላለፉት ረጅም ጊዜያት ሲደከምበት የቆየው የሕዝብ ውይይትና ልፋት ውጤታማ በሆነ መንገድ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋ የሚሆንበት ጊዜ በቅርብ እንደሚሆን አመላካች ነው። በሂደቱ ወቅት የሚነሱ ቅሬታዎችንና የተለያየ አስተያየት ያላቸውን ግለሰቦች፣ ቡድኖች ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳብ ለማስተናገድም ግልጽ የሆነ አሰራር የተቀረጸ ሲሆን፣ ይህም የውይይቱን ፍትሐዊነት የበለጠ ያጠናክረዋል። በአጠቃላይ፣ የ4ሺህ የሕዝብ ወኪሎች ንቁ ተሳትፎ እያደረጉበት የሚገኘው ይህ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በኢትዮጵያ የፖለቲካና ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ ይገኛል። የነገዋን ሀገር በጋራ መግባባት ላይ ለመገንባት የተጣለው መሠረትም ተጨባጭ ፍሬ የሚያፈራበት ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ምክክሩ ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ ቤት ሆና በጠንካራ መሰረት ላይ እንድትገነባ ያስችላል- ተመካካሪዎች
Aug 13, 2026 335
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ ቤት ሆና በጠንካራ መሰረት ላይ እንድትገነባ ያስችላል ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ዋናው ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ይገኛል። በምክክሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ነው፡፡ ይህ የምክክር ሂደት በኢትዮጵያ ጠንካራ የመግባባት ባህል በመገንባት የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ መሰረት እንደሚጥል ትልቅ ተስፋ ተጥሎበታል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡት ተመካካሪዎች መካከል ጌታቸው ቢነሳው እንዳሉት፣ ኢትዮጵያን ጠንካራ እና ልዩ የሚያደርጋት ብሔር ብሔረሰቦች በአንድነት፣ በመከባበር እና በመተሳሰብ የሚኖሩባት ድንቅ ሀገር መሆኗ ነው። ይህ ለዘመናት የቆየው የጸና ሕብረ ብሔራዊነት ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ ቤት ሆና በጠንካራ መሰረት እንድትገነባ የሚያስችል ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን አንስተዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሁላችንም ሀሳቦች በነፃነት ተደምረው የጋራ ሀገራችንን ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ተመካካሪዎች በመገንዘብ ለዘላቂ ሰላም፣ ዕድገት እና ሀገረመንግስት ግንባታ በንቃት በመሳተፍ ላይ እንገኛለን ብለዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ወይዘሮ እናና የኋላ፣ እየተካሄደ ያለው የምክክር ጉባኤ በሀገራችን የመጀመሪያው እና ታይቶ የማይታወቅ በመሆኑ የሕዝባችንን አንድነት ይበልጥ የሚያጠናክር ታሪካዊ ጉባኤ መሆኑን ተናግረዋል። እኛም በምክክሩ ለቀጣይ ትውልድ የሚመጥን ጠንካራ ሀገር ለማስተላለፍ ሀሳባችንን በግልጽነት እና በመከባበር እየሰጠን እንገኛለን ነው ያሉት። በአሁኑ ሰዓት ለሀገራችን ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ሁሉን አቀፍ እና ግልጽ የሆነ ምክክር ብቻ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ተስፋዬ አዳነ ናቸው። ይህም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ እና ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ጽኑ መሰረት ይጥላል ሲሉ ተናግረዋል። ተመካካሪዎችም በሰለጠነ አግባብ እና በሰከነ መንፈስ እየተደማመጥን ሀሳባችንን እየገለጽን እንገኛለን ብለዋል። ቀጣዩ ትውልድ የጸናች እና የበለጸገች ኢትዮጵያን መረከብ የሚችለው ዛሬ ለሀገራችን በሚበጁ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን ስንመካከር ብቻ መሆኑንም አንስተዋል።
ፖለቲካ
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው
Aug 14, 2026 46
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ) ፦ የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ የተቋማት አፈፃፀምን ጨምሮ፣ የሴፍቲኔት፣ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተከናወኑ ተግባራትና ሌሎች ኢኒሼቲቮችን ገምግሟል። የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው። ዛሬ ለአንድ ሰው የዘራነው ተስፋ ነገ ለማኅበረሰባችን የሚያፈራ ፍሬ ይሆናል፣ ዛሬ የረዳነው ወገን ነገ ሌላውን ለመርዳት የሚነሳ ዜጋ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። በጎ ፈቃድ አንድ ጊዜ የሚደረግ ተግባር ሳይሆን ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር የመልካምነት ባህል በመሆኑ ባህሉን በማዳበር ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል። በሌላ በኩል በክልሉ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የቅዳሜ ገበያዎችን ተደራሽ በማድረግ የተጀመሩ ተግባራትን ማጎልበት እንደሚገባ ገልፀዋል። ዜጎችን ከተረጂነትና ከጥገኝነት በማላቀቅ ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙ ምርታማነታቸውን በማሳደግ የተጀመሩ ተግባራትም ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ሁሉም አመራር የበኩሉን ሀላፊነት እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ የመንግስት እና የፓርቲ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በምክክር ጉባኤው እየተነሱ ያሉት ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው
Aug 14, 2026 39
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከተመካካሪዎች እየተነሱ የሚገኙ ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገትና የተሻለ መጻኢ ጊዜ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ተመካካሪ አበራ አኔቦ፤ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደፊት የሚያሻግሩና የጋራ ሀገርን መገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች ከተመካካሪዎች እየተነሱ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው ምክክር ለሀገራችን ዘላቂ ጥቅም የሚያስገኝ እና ለመጪው ትውልድም መልካም አርአያ የሚሆን ታሪካዊ ጉባኤ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ይህም ለኢትዮጵያ ቀጣይነት ላለው ዘላቂ ዕድገት ምቹ ዕድል ይዞ እንደሚመጣ ታላቅ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። ተመካካሪ ወይዘሮ ኦድንጊሊ ሎ፤ አካታች እና አሳታፊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እጅግ አስፈላጊ በሆነ ወቅት መከናወኑን ሂደቱም የተሳካና የኢትዮጵያን የወደፊት ጉዞ የሚያስቀጥሉ መልካም አጋጣሚዎችን መፍጠሩን ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያንን በተወካዮቻቸው በምልዓተ ያሳተፈ መሆኑንና ኢትዮጵያን አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስችሉ ጠቃሚ ሀሳቦች በነጻነት እንዲነሱ ምቹ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሀገሪቱን ብዝሃነት ያንጸባረቀ እና ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ አዎንታዊ የምክክር ጉባኤ እንደሆነም ነው ያነሱት። ሌላኛው ተመካካሪ ታደሰ ዳኜ በበኩላቸው፤ ለሀገር አንድነት ምክክር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝና መልካም ውጤት ይዞ ይመጣል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል። ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች የወከሉ ተመካካሪዎች በነጻነትና አሳታፊ በሆነ መልኩ እየተመካከሩ በመሆኑ ሀገራዊ ምክክሩ ውጤታማ ነው ብለዋል።
የምክክር ጉባኤው የዘመናት ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት ነው-ተመካካሪዎች
Aug 14, 2026 51
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታትና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ የጋራ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በምክክሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች፤ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የጋራ የመፍትሔ ሀሳብ የቀረበበት መሆኑን ተናግረዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ነኢ አለልኝ ምክክሩ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግር ጠቃሚ ግብአቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በሀገሪቱ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮች ላይ በስፋት ተመካክረን የመፍትሔ ሀሳቦችን አስቀምጠናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ኒሽራ ሱሌይማን ሀሳባችንን በነጻነትና በግልጽ በማቅረብ የመፍትሄ ሀሳቦች ላይ ምክክር እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። ምክክሩ መግባባት የሰፈነባት ያደገችና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ምክክሩ ለሀገር የሚበጁ ጠቃሚ ግብዓቶች የተገኙበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ደራራ ጣፋ ናቸው።
የስራ ቡድኖች የአጀንዳ ምክረሃሳቦቻቸውን ለሚያደራጀው ቡድን እያቀረቡ ነው
Aug 14, 2026 67
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የስራ ቡድኖች ሁሉም ቡድኖች ያዘጋጇቸውንና የተስማሙባቸውን ምክረ-ሀሳቦች እንዲያናብብ፣ እንዲያጣጥም እና እንዲያደራጅ ለተቋቋመው እና 120 አባላት ላሉት ቡድን በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡ ይህ ቡድን ከስምንቱ ባለ 500 አባላት የስራ ቡድን በተመረጡ 15 አባላት የተዋቀረ ሲሆን መግባባት የተደረሰባቸውን የሁሉንም አጀንዳዎች ምክረሃሳቦች አዳምጦ የሚያጣጥም፣ በሚቀርቡ ሀሳቦች መካከል መጣረስ እንዳይኖር ጥንቃቄ የሚያደርግና ለጠቅላላ ሀሳቦቹ ወጥነት በመፍጠር 4ሺ አባላት ላሉት ዋናው ጉባኤተኛ አደራጅቶ የሚያቀርብ ነው፡፡ ቡድኑ በአሁኑ ሰዓት ከእያንዳንዱ የስራ ቡድን የመጡ ምክረሃሳቦችን በማዳመጥ ላይ መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያን በሀገራዊ አጀንዳዎቻቸው ላይ በጋራ የሚመክሩበትን ዕድል ፈጥሯል
Aug 13, 2026 296
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያን በሀገራዊ አጀንዳዎቻቸው ላይ በጋራ የሚመክሩበትን ዕድል መፍጠሩን ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያን ለዘመናት ሲፈትኗት የቆዩ ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልዩነቶችና አለመግባባቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በንግግር ለመፍታት የሚያስችል እድል ተፈጥሯል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤም ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር የሚችሉበትን ታሪካዊ ምዕራፍ ከፍቷል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ዋናው ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲካሄድ ቆይቶ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ተመካካሪ ቄስ ተሻለ አለባቸው ለኢዜአ እንዳሉት፤ ጉባኤው በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በስፋት እየመከረ ነው፡፡ በየደረጃው ያሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች የታደሙበት፣ የሀሳብ ብዝሃነት የሚስተናገድበት አካታችና አሳታፊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምክክሩ ለዘመናት የኢትዮጵያውያን የልዩነት ምንጭ ሆነው የዘለቁ አጀንዳዎችን የያዘ መሆኑን ገልጸው፤ ለሀገር የሚበጁ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩበት ነውም ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተጀመረው ምክክር ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ ለቀጣዩ ትውልድ ተሞክሮ እንደሚወሰድበት ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በዓድዋና በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ የጻፍነውን አኩሪ ታሪክ በምክክሩ ላይ በመድገም ለትውልድ አሻራ አስቀምጠን እናልፋለን ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ተመካካሪ ድንቅነሽ ኡባራ በበኩላቸው፤ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ተመካካሪዎች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ለሀገር ይጠቅማል ያሉትን የየራሳቸውን ሀሳብ ማንጸባረቃቸውን ገልጸው፤ ጉባኤው በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መፍትሔ ማስቀመጥ እንደሚቻል አመላክቷል ብለዋል፡፡ ጉባኤው ዜጎች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር የሀገር ሁለንተናዊ ልማት እንቅፋቶችን በማለፍ ለነገው ትውልድ የተሻለች ሀገር ማስረከብ የሚያስችል ምቹ ምኅዳር መፍጠሩን የገለጹት ደግሞ ተመካካሪ አበራሽ አባይነህ ናቸው፡፡ ተመካካሪዎች መደማመጥን መርህ በማድረግ ለምክክር በተመረጡ አጀንዳዎች ላይ አንድነትን የሚያጠናክሩ ሀሳቦችን መሰንዘራቸውን ገልጸው፤ ሀገርን የሚያጸና መፍትሔ እንደሚመጣ ተስፋ ሰንቄያለሁ ብለዋል፡፡
በ8 የአጀንዳ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲመካከሩ የቆዩት የአጀንዳ ቡድኖች መግባባት ላይ ደረሱ
Aug 13, 2026 300
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ከሁለት ቀናት በፊት በሰላም ግንባታ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በመንግስት አደረጃጀት እና የፖለቲካ ስርዓት ሲመካከሩ የነበሩ ቡድኖ መግባባት ላይ እንደደረሱ መገለፁ የሚታወስ ነው፡፡ በዛሬው ዕለትም የተቀሩት ማለትም በሀገር ግንባታ ፣በፌዴራል ከተሞች ጉዳይ፣ ተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነት እና ሰብዓዊ መብት፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተመካካሪዎች ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
የኢትዮጵያውያን ታሪካዊ የጋራ ውል
Aug 13, 2026 274
በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አሁን ላይ የሕዝቡን የጋራ እይታ ወደሚያንጸባርቁ ተጨባጭ የምክረ-ሃሳብ ሰነድ በመቀየር ላይ ይገኛል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ያለውና ነገ አንድ ወሩን የሚደፍነው ይህ ታሪካዊ ጉባኤ፣ የልዩነቶችን በር እየዘጋ የጋራ ወደሆኑ መፍትሔዎች እየተሸጋገረ ይገኛል። በጉባኤው ላይ ከሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች የተወጣጡ 4ሺህ የሕዝብ ወኪሎች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ፣ ይህም የውይይቱን አሳታፊነትና ህዝባዊ መሰረት በእጅጉ የሚያጎላ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዋናው ጉባኤው የሚሆኑ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ በማድረግ ወደ ውይይት ተገብቷል። እነዚህም አጀንዳዎች የሀገር ግንባታን፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽን፣ የፖለቲካና የምርጫ ሥርዓትን፣ የፌዴራል ከተሞች ጉዳይን፣ የሃይማኖት ጉዳዮችን፣ የተቋማት ግንባታን፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶችን፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን፣ የሙስናና መልካም አስተዳደር ችግሮችን እንዲሁም የሰላም ግንባታን ያካተቱ ናቸው። እያንዳንዱ አጀንዳ በ500 አባላት በተደራጁ ስምንት ልዩ የሥራ ቡድኖች ተከፍሎ ሲመካከርባቸው ቆይቷል። ባለፉት ሳምንታት በተካሄዱት ተከታታይ ውይይቶች ተሳታፊዎች እርስ በእርስ በመደማመጥ፣ ልዩነቶችን በመሰብሰብ እና ወደ አማካይ ሃሳብ በመምጣት በኩል ትልቅ እርምጃ ማሳየት ችለዋል። ተሳታፊዎቹ በመግባባት የተዘጋጁትን የተጠናከሩ ምክረ-ሃሳቦች በመቀበልና የቃለ-ጉባኤ ሰነዶችን በመፈራረም ለወደፊቱ የሀገሪቱ አቅጣጫ መሠረት የሚሆን የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። የሥራ ቡድኖቹ የመጀመሪያ ምዕራፍ ስራቸውን በማጠናቀቃቸው፣ አሁን ሂደቱ ወደ ሁለተኛውና ወሳኙ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተበታተኑትንና በተለያዩ ቡድኖች የቀረቡትን ምክረ-ሃሳቦች ወጥነት ባለው መልኩ ለማደራጀትና ለማጣጣም ስምንት ልዩ ቡድኖች ተዘጋጅተዋል። የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ የሂደቱ አጠቃላይ ሂደት ሦስት አራተኛ ያህል መጠናቀቁ ላለፉት ረጅም ጊዜያት ሲደከምበት የቆየው የሕዝብ ውይይትና ልፋት ውጤታማ በሆነ መንገድ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋ የሚሆንበት ጊዜ በቅርብ እንደሚሆን አመላካች ነው። በሂደቱ ወቅት የሚነሱ ቅሬታዎችንና የተለያየ አስተያየት ያላቸውን ግለሰቦች፣ ቡድኖች ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳብ ለማስተናገድም ግልጽ የሆነ አሰራር የተቀረጸ ሲሆን፣ ይህም የውይይቱን ፍትሐዊነት የበለጠ ያጠናክረዋል። በአጠቃላይ፣ የ4ሺህ የሕዝብ ወኪሎች ንቁ ተሳትፎ እያደረጉበት የሚገኘው ይህ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በኢትዮጵያ የፖለቲካና ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ ይገኛል። የነገዋን ሀገር በጋራ መግባባት ላይ ለመገንባት የተጣለው መሠረትም ተጨባጭ ፍሬ የሚያፈራበት ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ምክክሩ ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ ቤት ሆና በጠንካራ መሰረት ላይ እንድትገነባ ያስችላል- ተመካካሪዎች
Aug 13, 2026 335
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ ቤት ሆና በጠንካራ መሰረት ላይ እንድትገነባ ያስችላል ሲሉ ተመካካሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ዋናው ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ይገኛል። በምክክሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ነው፡፡ ይህ የምክክር ሂደት በኢትዮጵያ ጠንካራ የመግባባት ባህል በመገንባት የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ መሰረት እንደሚጥል ትልቅ ተስፋ ተጥሎበታል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡት ተመካካሪዎች መካከል ጌታቸው ቢነሳው እንዳሉት፣ ኢትዮጵያን ጠንካራ እና ልዩ የሚያደርጋት ብሔር ብሔረሰቦች በአንድነት፣ በመከባበር እና በመተሳሰብ የሚኖሩባት ድንቅ ሀገር መሆኗ ነው። ይህ ለዘመናት የቆየው የጸና ሕብረ ብሔራዊነት ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ ቤት ሆና በጠንካራ መሰረት እንድትገነባ የሚያስችል ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን አንስተዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሁላችንም ሀሳቦች በነፃነት ተደምረው የጋራ ሀገራችንን ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ተመካካሪዎች በመገንዘብ ለዘላቂ ሰላም፣ ዕድገት እና ሀገረመንግስት ግንባታ በንቃት በመሳተፍ ላይ እንገኛለን ብለዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ወይዘሮ እናና የኋላ፣ እየተካሄደ ያለው የምክክር ጉባኤ በሀገራችን የመጀመሪያው እና ታይቶ የማይታወቅ በመሆኑ የሕዝባችንን አንድነት ይበልጥ የሚያጠናክር ታሪካዊ ጉባኤ መሆኑን ተናግረዋል። እኛም በምክክሩ ለቀጣይ ትውልድ የሚመጥን ጠንካራ ሀገር ለማስተላለፍ ሀሳባችንን በግልጽነት እና በመከባበር እየሰጠን እንገኛለን ነው ያሉት። በአሁኑ ሰዓት ለሀገራችን ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ሁሉን አቀፍ እና ግልጽ የሆነ ምክክር ብቻ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ተስፋዬ አዳነ ናቸው። ይህም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ እና ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ጽኑ መሰረት ይጥላል ሲሉ ተናግረዋል። ተመካካሪዎችም በሰለጠነ አግባብ እና በሰከነ መንፈስ እየተደማመጥን ሀሳባችንን እየገለጽን እንገኛለን ብለዋል። ቀጣዩ ትውልድ የጸናች እና የበለጸገች ኢትዮጵያን መረከብ የሚችለው ዛሬ ለሀገራችን በሚበጁ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን ስንመካከር ብቻ መሆኑንም አንስተዋል።
ማህበራዊ
የመደመር መንግስት የፈጠራቸውን መልካም እድሎች በመጠቀም ብልሹ አሰራሮችን መዋጋት ይገባል
Aug 14, 2026 14
አዳማ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የመደመር መንግስት የፈጠራቸውን መልካም እድሎች በመጠቀም ለሀገር ልማት በጋራ መትጋትና ብልሹ አሰራሮችንም መዋጋት ይገባል ሲሉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቴ አለነ ገለጹ። የፌዴራል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓል ማጠቃለያ መድረክ "የፀረ ሙስና ትግል ትናንት ዛሬ እና ነገ በሚል መሪ ሀሳብ" በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቴ አለነ፤ የሙስና ትግል የመጀመሪያ ምዕራፍ መከላከልን፣ ምርመራንና ክስን በአንድ ተቋም በማድረግ ይሰራ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም እንቅስቃሴው ህዝብን የትግሉ ባለቤት ያላደረገ፣ የሙስና መከላከል ስራን የረሳና ለትውልድ የስነ-ምግባር ግንባታ ቦታ የማይሰጥ ነበር ብለዋል። በሁለተኛው ምዕራፍ፣ ከሚሊኒየሙ መባቻ ጀምሮ ለውጡ እስከመጣበት ጊዜ ድረስ የነበረው ወቅት በልማታዊ መንግስት ስም ከፍተኛ ጣልቃገብነት የተካሄደበት እንዲሁም ሙስና በከፍተኛ ሁነታ የተስፋፋበት እንደነበር አንስተዋል። በዚህም ምክንያት የህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ ሜጋ የመንግስት ፕሮጀክቶች በሙስና እና በሌብነት ምክንያት ለከፍተኛ ችግር ተዳርገው እንደነበር አውስተዋል። በሶስተኛው ምዕራፍ፣ ማለትም ከሀገራዊ ለውጡ መባቻ ጀምሮ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ ከሙስና ትግል አኳያ መሰረታዊ ለውጥ መደረጉን ገልጸዋል። በኮሚሽኑ ላይ ከተደረጉት ማሻሻያዎች መካከል ዋነኛው የህግ ሪፎርም መሆኑን አንስተው፤ ሙስናን በአንድ ተቋም ብቻ መታገል ስለማይቻል ሁሉም የመንግስት ተቋማት የትግሉ ባለቤት እንዲሆኑ መደረጉን አብራርተዋል። በሶስቱም የመንግስት አካላት መካከል ጥብቅ የመረጃ ቅብብሎሽ፣ ጠንካራ ትስስር እና ቅንጅት እንዲፈጠር የሚያስችል ለውጥ ተደርጓል ብለዋል። ይህም ስርዓታዊ እና መንግስታዊ ሙስና መሰረት እንዳይኖረውና እንዳይፈጠር ለማድረግ የሚያስችል የሚያበረታታ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የዲጂታላይዜሽንን መልካም እድሎች በመጠቀም አገልግሎቶችን ከሰው ንክኪ ነፃ እና አካታች በሆነ መንገድ ማቅረብ መቻሉ፣ መሰረታዊ የእሳቤ ለውጥ ማምጣቱንና ለፀረ-ሙስና ትግሉ ጠንካራ መሰረት እየጣለ እንደሚገኝ አክለው ገልጸዋል። በእነዚህ አዎንታዊ ለውጦች እና የመደመር እሳቤ በፈጠራቸው አዳዲስ እድሎች በመጠቀም፣ በአሁኑ ወቅት ሙስና ጎልቶ በሚታይባቸው ዘርፎች ላይ ያተኮረ ዘመቻ መጀመሩን ለአብነት አንስተዋል። በመሆኑም የተጀመሩ አዎንታዊ ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል፣ በመጪው ጊዜም ያልተቋረጠና የተቀናጀ የሙስና ትግል ማድረግ እንደሚገባ አቶ እውነቴ አሳስበዋል። የፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ እሸቴ አስፋው በበኩላቸው፣ ባለፉት ዓመታት ኮሚሽኑ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የሚያስችሉ ስትራቴጂዎችን ነድፎ ሲንቀሳቀስ መቆየቱንና በዚህም አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። 25ኛ ዓመታችንን ስናከብርም ጠንካራና ደካማ ጎኖቻችንን ነቅሰን በማውጣት በቀጣይ የተሻለ ሥራ ለመሥራት ዝግጁነታችንን እያረጋገጥን ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ የሙስና እና የብልሹ አሰራር ችግሮችን በመፍታት፣ ተጠያቂነትን በማስፈንና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸውን ተግባራት ለማሳለጥ በሚያስችል ጠንካራ ቁመና ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በተለይም ከሀብት ምዝገባ አንጻር አዎንታዊ ለውጦች መኖራቸውን ያነሱት ምክትል ኮሚሽነሩ፣ ሀብታቸውን ባላስመዘገቡ አካላት ላይ ተጠያቂነትን የማስፈን ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በመድረኩ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶን ጨምሮ ከፌዴራልና ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ስርዓቷን ወደ ራስ ገዝ አስተዳደር ለማሸጋገር መሠረታዊ ለውጥ እያደረገች ነው
Aug 13, 2026 353
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ስርዓቷን ወደ ራስ ገዝ አስተዳደር ለማሸጋገር መሠረታዊ ለውጥ እያደረገች መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ ገለጹ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጆን ኤፍ ኬኔዲ መታሰቢያ ቤተ-መጽሐፍት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ተከብሯል፡፡ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያና አሜሪካ ሁሉን አቀፍ ትብብርና አጋርነት ከምዕተ ዓመት የተሻገረ ነው፡፡ በኢትዮጵያና አሜሪካ መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ትብብር በተቋም ግንባታ፣ ቴክኒክ ድጋፍ፣ በአካዳሚክ አቅም ልማት፣ በምርምር እና የተቋማዊ ለውጥ ላይ ያተኩረ መሆኑን ገልጸው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ትብብሩ ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ አካዳሚያዊ ነፃነትን ለማረጋገጥ፣ የትምህርት ጥራትንና ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ስርዓቷን ወደ ራስ ገዝ አስተዳደር በማሸጋገር ሂደት ላይ መሆኗን ገልጸዋል፡፡ አሜሪካ ለዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ አመራር ልማት እና ለተቋማት አደረጃጀት የሰነድ ዝግጅት ድጋፍ ስታደርግ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ፣ ጠንካራ እና ዘላቂ ሁሉን አቀፍ ትብብር አላቸው ብለዋል፡፡ የሁለቱ ሀገራት በትምህርት ዘርፍ ያላቸው አጋርነት የላቀ መሆኑን በማንሳት፤ የጆን ኤፍ ኬኔዲ ቤተ-መጽሐፍት አንዱ የትብብራቸው ምልክት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ማህበረሰብ ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ ለበርካታ ዓመታት ተማሪዎችን፣ ምሁራን እና ተመራማሪዎችን ሲያገለግል ቆይቷል ብለዋል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በግብርና፣ በህብረተሰብ ጤናና በሥራ ፈጠራ ዘርፎች የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንና የጋራ የምርምር ፕሮጀክቶችን እየደገፉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ ራስ ገዝነት አስተዳደር በሚያደርጉት ሽግግር አሜሪካ አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ጀይሉ ዑመር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ታሪካዊውን የጆን ኤፍ ኬኔዲ መታሰቢያ ቤተ-መጽሐፍት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ማክበር ትልቅ ክብር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የጆን ኤፍ ኬኔዲ መታሰቢያ ቤተ-መጻሕፍት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት፣ የምርምርና የእውቀት ልውውጥ የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡ ቤተ መጻሕፍቱ ትውልድ ተኮር ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ተማሪዎችንና ምሁራንን በማፍራት የትምህርት ዕድገትና የባህል ጥበቃ መሰረት ሆኖ ማገልገሉን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያና አሜሪካ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዘርፍ ያላቸውን የቆየ ተቋማትን የማጠናከር፣ የትምህርት ዕድል የማስፋትና የምርምር አጋርነት ያጠናክራልም ብለዋል፡፡
በክረምቱ ማጠቃለያ ወቅት የሚያጋጥመውን የደም እጥረት ለመቀነስ ያለመ የደም ልገሳ መርሃ ግብር ይካሄዳል
Aug 13, 2026 252
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በክረምቱ ማጠቃለያ ወቅት የሚያጋጥመውን የደም እጥረት ለመቀነስ ያለመ የደም ልገሳ መርሃ ግብር መዘጋጀቱ ትልቅ ጠቀሜታ አለው ሲሉ የኢትዮጵያ ደምና ሕብረ ሕዋስ ባንክ የደም ለጋሾች ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር መላሽ ገላው ገለጹ። ሀገር አቀፍ የበጎ ፈቃድ የደም ልገሳ ዘመቻ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደምና ሕብረ ሕዋስ ባንክ አገልግሎት እና በሙስሊም ተማሪዎች ሊግ (MS League) ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፤ ከነሐሴ 21 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ ነው። የኢትዮጵያ ደምና ሕብረ ሕዋስ ባንክ የደም ለጋሾች ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር መላሽ ገላው ሀገር አቀፍ የበጎ ፈቃድ የደም ልገሳ ዘመቻ አስመልክቶ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት፤ ዘመቻው የሚካሄድበት የነሐሴ መጨረሻ ወቅት የደም ክምችት የሚቀንስበት በመሆኑ መርሐ ግብሩ ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ይኖረዋል። ስለሆነም ወጣቱም ሆነ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በዚህ የደም ልገሳ ዘመቻ መርሐ ግብር ላይ በንቃት በመሳተፍ የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። የሙስሊም ተማሪዎች ሊግ የዑምራ ሰብ-ቻፕተር አመራርና የደም ልገሳ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ አክረም መሐመድ በበኩላቸው፤ በሀገሪቱ በሚገኙ የጤና ተቋማት ውስጥ የሚያጋጥመውን የደም እጥረት ለመቀነስ እና የእናቶች፣ የአደጋ ተጎጂዎችና የካንሰር ታካሚዎችን ሕይወት ለመታደግ ዘመቻው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በየዕለቱ ደም ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ለመድረስ ርብርብ በማድረግ የሚጠበቅብንን ለማበርከት ዘመቻው አስፈላጊ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። የደም ልገሳ ዘመቻ መርሐ ግብሩ በአዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
የፍትህ ስርዓቱን ተደራሽነትና አካታችነት ለማረጋገጥ በማህበረሰብ ፍትህ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል
Aug 13, 2026 243
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦የፍትህ ስርዓትን ተደራሽነትና አካታችነት ለማረጋገጥ ከመደበኛው ባለፈ በማህበረሰብ ፍትህ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን የፍትሕ ሚኒስቴር ገለፀ። የፍትሕ ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር ያዘጋጀውን የኢትዮጵያ ቤተሰብ ፍትሕ መምሪያ ይፋ አደረገ። የኢትዮጵያ ቤተሰብ ፍትሕ መምሪያው ለቤተሰብ፣ ሕጻናትና ተጋላጭ ወገኖች የሕግ ጥበቃን ለማረጋገጥና ማህበራዊ ፍትሕን ለማስፈን የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል። መምሪያው በቤተሰብ ጉዳዮች ዙሪያ የሚነሱ የሕግ ጉዳዮችን በማስረጃና በተግባር ላይ በተመሠረተ አሠራር በመምራት መፍትሔ ለመስጠት እንደሚያግዝ ተመላክቷል። የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የፍትህ ስርዓቱን በመደበኛውና ከመደበኛው ውጭ ተደራሽነትና አካታችነት ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል። የባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ማጠናከርና ማስፋት የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው፤ በዘጠኝ ክልሎችና በአንድ ከተማ አስተዳደር ባህላዊ ፍርድ ቤቶች እውቅና አግኝተው እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል። በፍርድ ቤቶች ከሚቀርቡ ጉዳዮች መካከል በአራተኛ ደረጃ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዙት ከቤተሰብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ናቸው። መምሪያውም በቀለብ፣ በልጆች አስተዳደግና ጉብኝት፣ በንብረት አስተዳደር፣ በፍቺና በንብረት ክፍፍል እንዲሁም ከቤተሰብ ጉዳዮች ጋር በተያያዙ የሕግ ጉዳዮች ላይ የሚመራና የሚዳስስ መሆኑን ተናግረዋል። ለቤተሰብ፣ ሕጻናትና ተጋላጭ ወገኖች የሚደረገውን የሕግ ጥበቃ ለማረጋገጥና ማህበራዊ ፍትሕን ለማስፈንም መምሪያው ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ቤተሰብ ፍትሕ መምሪያው ከዳኞች፣ ከትምህርት ተቋማትና ከባለድርሻ አካላት በተውጣጡ ባለሙያዎች ኮሚቴ በማቋቋም የተዘጋጀ መሆኑን አንስተዋል። የመምሪያው ዝግጅት ሂደትም በማስረጃና በተግባር ላይ የተመሠረተ አሠራርን በመከተል መዘጋጀቱን አስታውቀዋል። የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ልዑል ካህሳይ በበኩላቸው፤ መምሪያው ባለሙያዎች የተቀራረበ የህግ አተረጓጎም እንዲኖራቸው በማድረግ ለፍርድ ቤቶች አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል። የሄግ የሕግ ፈጠራ ኢንስቲትዩት ዋና ስራ አስፈፃሚ ሼከር ፑላ በበኩላቸው፤ መምሪያው የማህበረሰብ ፍትህን በማስፋት ሰዎች በአቅራቢያቸው ፍትህን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል። መምሪያው መልካም ተሞክሮዎችን በማጋራት ከቤተሰብ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ክርክሮችን ፍትሃዊ በሆነ አግባብ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ የመምሪያው የባለሙያ ኮሚቴ አባልና የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህግ መምህር ንጉሴ አፈሻ(ዶ/ር) ናቸው።
ኢኮኖሚ
ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል የማመንጨት አቅሟን በማሳደግ የቀጣናው የኃይል ማዕከል እየሆነች ነው
Aug 14, 2026 43
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ማመንጨት አቅሟን በማሳደግ የቀጣናው የኃይል ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ የውሃ፣ የፀሐይ፣ የነፋስና የጂኦተርማል ብዝኅ የኃይል ፀጋዎች ልማት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅምን ማጎልበት የሚቻልበት ምኅዳር እየፈጠረ ይገኛል። የታዳሽ ኃይል ልማት እመርታዊ ጉዞም የኤሌክትሪክ ማመንጨትን ከልማት፣ ልማትን ከኢኮኖሚ ዕድገት፣ ኢኮኖሚ ዕድገትን ከቀጣናዊ ትስስር ጋር እያሰናሰለ የሚገኝ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ግብ ነው። ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፣ የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር ዘላቂ ኢኮኖሚ እንድትገነባ እያስቻለ ነው። የታዳሽ ኃይል ምንጮቹን በማቀናጀት የሚካሄደው ልማትም የኢንዱስትሪ፣ የግብርና፣ የከተማ ልማትና የዲጂታል ኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የኃይል መሠረተ ልማት እየገነባ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የውሃ፣ የፀሐይ፣ የነፋስና የጂኦተርማል ሃብቶችን በማልማት የኤሌትክትሪክ የኃይል ምንጮችን፣ ደህንነትና ዘላቂነትን በማጎልበት የኢኮኖሚ መሠረት መፍጠር እየተቻለ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በዜጎች ትብብርና በሀገር አቅም የተገነባው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ የኃይል ልማት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን አስረድተዋል። የሕዳሴ ግድብ የኃይል አቅርቦት አቅም የኢትዮጵያን ፍላጎት ለማሟላት ከማገዙ ባሻገር፣ ኃይልን ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ የቀጣናዊ ኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር አዲስ ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። ይህም ኃይል ለኢትዮጵያ ዕድገትና ልማት የሚውል ግብዓት ብቻ ሳይሆን የንግድ፣ የዲፕሎማሲና የቀጣናዊ ትብብር መሣሪያ እየሆነ መምጣቱን እንደሚያመላክት አብራርተዋል። የዓለም አቀፍ የውሃና የኃይል ገበያ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታን ታሳቢ በማድረግም ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ፀጋዎቿን በማልማት ከሀገር ውስጥ የኃይል ፍላጎት ባሻገር ቀጣናዊ ትስስርን እያሰፋች መሆኗን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት እመርታዊ ጉዞም ኃይልን ከማመንጨት የተሻገረ ቀጣናዊ የጋራ ዕድገትና ብልፅግናን የማፋጠን አህጉራዊ የልማት ግብ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በዚህም ስትራቴጂካዊ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የራሷን የኃይል ደህንነት ከማረጋገጥ ባሻገር ለምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስርና ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ውህደት የሚያግዝ አዲስ ምዕራፍ እየገነባች ነው ብለዋል። ለአብነትም ከጅቡቲ፣ ኬንያና ሌሎች ጎረቤቶች ጋር ያለውን የኃይል ትስስር በማስፋፋት የጋራ ዕድገትና ብልፅግናን የሚያጎለብቱ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። በቀጣይም ደቡብ ሱዳንና ሶማሊያን ጨምሮ ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብና የኃይል ትስስር መሠረተ ልማትን ለማስፋፋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። የኃይል ሽያጩም ኢትዮጵያን የኃይል ማዕከል በማድረግ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ምንጭ በመሆን ጭምር ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጋር ተሰናስሎ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው የበልግ ወቅት ከለማው መሬት እስካሁን ከ21 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል
Aug 14, 2026 57
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው የበልግ እርሻ በዘር ከተሸፈነው መሬት ውስጥ እስካሁን ከ21 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በኦሮሚያ ክልል የበልግ እርሻ ልማት ለአርሶና አርብቶ አደሩ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ምንጭና የምግብ ዋስትና መሰረት ነው። በክልሉ በበልግ ዝናብ የሚከናወነው ይህ የግብርና እንቅስቃሴ አርሶ አደሩ የምግብ ፍላጎቱን እንዲሸፍን ከማስቻሉም በላይ፣ ገበያን ለማረጋጋት የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው። በተለይም እንደ ቦረና፣ ጉጂና አርሲ ባሉ አካባቢዎች በበልግ እርሻው የከብት መኖን ከማልማት ባሻገር ዋና ዋና የህብረተሰቡ የፍጆታ ሰብሎች የሚመረቱበት በመሆኑ ለክልሉ ግብርና መነቃቃት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። ክልሉ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና የሜካናይዜሽን አጠቃቀምን በማስፋት፣ የአርሶ አደሩን የሙያ ብቃት በማሳደግ እና የግብርና ግብዓቶችን በወቅቱ በማቅረብ ረገድ ያሳየው ቁርጠኝነት ለአፈፃፀሙ መሳካት ዋና ምክንያት ሆኗል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በበልግ ወቅት ወደ ሁለት ሚሊዮን ሄክታር የሚጠጋ መሬት በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ለምቶ ወደ ምርት መሰብሰብ ተገብቷል። ለበልግ እርሻው ውጤታማነት ለአርሶ አደሩ የሙያ ብቃትን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች የተሰጡ ሲሆን፣ ባለሙያዎች በመስክ በመገኘት ያልተቋረጠ ሙያዊ ድጋፍና ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ምርትና ምርታማነትን የሚጨምሩ የግብርና ግብዓቶች በወቅቱ ለአርሶ አደሩ እንዲደርሱ መደረጉን ጠቁመው፤ ከዚህ በተጨማሪም ሰብሉን ከተባይና ከአረም ለመጠበቅ የሚያስችሉ የፀረ-ተባይና የፀረ-አረም መድሃኒቶች አቅርቦት መመቻቸቱን ገልጸዋል። በዚህም በዘንድሮው የበልግ እርሻ በዘር ከተሸፈነው መሬት ውስጥ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር በላይ በሚሆነው ላይ የደረሱ ሰብሎች የተሰበሰቡ ሲሆን፣ ከዚህም 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ማግኘት መቻሉን ገልጸዋል። የምርት አሰባሰቡን ቀልጣፋና ከብክነት የጸዳ ለማድረግ በግብርና ሜካናይዜሽን አማካኝነትና የሰው ኃይልን በማቀናጀት እየተካሄደ እንደሚገኝ አንስተዋል። እስካሁን ከተሰበሰቡት ዋና ዋና ሰብሎች መካከል፡ ጤፍ፣ስንዴ፣ገብስ፣ሰሊጥ፣ማሾ እና ሌሎችም ይገኙበታል ብለዋል። በኦሮሚያ ክልል የበልግ እርሻው በስፋት የተካሄደው በ11 ዞኖች ውስጥ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል የቦረና፣ ጉጂ፣ ምዕራብ አርሲ፣ ባሌ እና የምስራቅ ሐረርጌ ዞኖች በዋናነት ተጠቃሽ መሆናቸውን አክለዋል። በቀጣይም ቀሪዎቹን የሰብል ምርቶች በወቅቱና ያለ ብክነት ለመሰብሰብ የተጀመረው የተቀናጀ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ቢሮው አስታውቋል።
በካፋ ዞን የሌማት ትሩፋት መርሀግብር የአርሶ አደሮችን ገቢ እያሳደገ ነው
Aug 14, 2026 52
ቦንጋ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ በሌማት ትሩፋት መርሀግብር የተሰማሩ አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነታቸው እያደገ በመምጣቱ ተጨማሪ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናገሩ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ በበኩሉ በክልሉ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ውጤታማ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ምርትና ምርታማነት እያደገ መምጣቱን አስታውቋል። በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ መሻማሊ ቀበሌ በዓሣ ልማት ላይ የተሰማሩት አርሶ አደር አባቢያ አባጨብሳ እንዳሉት፤ በሌማት ትሩፋት መርሀግብር በጓሯቸው ለአሣ እርባታ የሚሆን ኩሬ በማዘጋጀት አሣ እያመረቱ ነው፡፡ ምርቱን ለቤት ውስጥ ፍጆታ ከማዋል ባለፈ ለሽያጭ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። መንግስታዊ ካለሆነ ድርጅት በተደረገላቸው ድጋፍ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር ተጨማሪ ኩሬዎችን በማዘጋጀት የዓሣ ልማት ሥራቸውን ማስፋፋታቸውን ገልጸዋል። በወረዳው ሒንጊዶ ቀበሌ በዶሮ እርባታ ሥራ የተሰማሩት አርሶ አደር ብርሃኑ ወልደሰንበት በበኩላቸው፣ ከዚህ ቀደም በባህላዊ መንገድ ዶሮዎችን ሲያረቡ ለአውሬ ይጋለጡ እና የእንቁላል ምርታቸውም ዝቅተኛ እንደነበር ተናግረዋል። አሁን ግን ባገኙት ሙያዊ ድጋፍ ታግዘው የዶሮ ቤት በማዘጋጀትና የተመጣጠነ መኖ ተጠቅመው በማርባታቸው የእንቁላል ምርትና ምርታማነትን ማሳደጋቸውን ገልጸዋል። ያመረቱትን እንቁላል ለቤት ውስጥ ፍጆታ ከማዋል ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል። በንብ ማንብ ሥራ ላይ የተሰማሩት የዶማ ቀበሌ አርሶ አደር ዳንኤል ቶሌ በበኩላቸው፣ በአምስት ባህላዊ ቀፎዎች ሥራ እንደጀመሩ ገልፀው የሌማት ትሩፋት መርሀግብር ሥራቸውን ለማስፋፋት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። በመርሀግብሩ በተደረገላቸው የንብ ቀፎና ሙያዊ ድጋፍ ታግዘው በአሁኑ ወቅት ከ50 በላይ ዘመናዊና ባህላዊ ቀፎዎች እንዳሏቸው ገልፀዋል። ከዚህም በዓመት ሁለቴ ማር እንደሚሰበስቡ ገልጸው፣ በአንድ ዙር ብቻ ከሚሰበስቡት የማር ምርት እስከ 168 ሺህ ብር ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሌማት ትሩፋት መርሀግብር ከተጀመረ ወዲህ በክልሉ 2ሺህ 763 የወተት፣ የዶሮ፣ የዓሣ፣ የማር እና የከብት ሥጋ መንደሮችን በማደራጀት ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ የገለጹት ደግሞ በክልሉ ግብርና ቢሮ የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ታመነ በቀለ ናቸው። መንደሮችን ከማደራጀት ባለፈ ለአርሶ አደሩ ስልጠና በመስጠት፣ በግብዓት አቅርቦት እንዲሁም የተጠናከር የድጋፍና ክትትል ሥራ በመሰራቱ በሁሉም ፓኬጆች ጥሩ መሻሻሎች ታይተዋል ብለዋል፡፡ በተለይም የዝርያ ማሻሻያ ፣ የአረንጓዴና ምጥን መኖ ልማትና አቅርቦት ላይ ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ መጠን ማሳደጉን አቶ ታመነ ተናግረዋል። በዚህም የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ከመጀመሩ በፊት በክልሉ በዓመት ይመረት የነበረው የወተት ምርት ከ307 ወደ 392 ሚሊዮን ሊትር ከፍ ማለቱን ጠቁመዋል። የእንቁላል ምርትን ከ335 ወደ 362 ሚሊዮን፣ የማር ምርት ከነበረበት 66 ሺህ ቶን ወደ 79 ሺህ ቶን እንዲሁም የዓሣ ሥጋ ምርትን ከ4ሺህ 615 ቶን በአማካይ ወደ 7ሺህ ቶን ለማሳደግ ተችሏል ብለዋል። ምርታማነት ማደጉም የህብረተሰቡ የምግብና ስነምግብ ሥርዓት እንዲሻሻል ከማድረግ ባለፈ ተኪ ምርትና የኤክስፖርት ምርቶች በመጠንና በጥራት እንዲያድጉ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል። በቀጣይም በተቀናጀ መልኩ የተጀመሩ ሥራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል የተሻለ ምርት በብዛትና በጥራት በማምረት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና የኩታ ገጠም አሠራርን በመጠቀማችን ምርታማነታችን ጨምሯል-አርሶ አደሮች
Aug 14, 2026 43
ጋምቤላ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና የኩታ ገጠም አሠራርን በመጠቀማችን ምርታማነታችን ጨምሯል ሲሉ በጋምቤላ ክልል የአኙዋ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ። አርሶ አደሮቹ፤ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና የኩታ ገጠም አሠራርን በመጠቀማቸው ምርታማነታቸው ጨምሮ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው ማደጉን ለኢዜአ ገልጸዋል። በዞኑ የአቦቦ ወረዳ ሞዴል አርሶ አደር ወይዘሮ አጁሉ ኪሩ በሰጡት አስተያየት፤ ቀደም ሲል በባህላዊ የአስተራረስ ዘዴ ሲያለሙ ከራስ ፍጆታ ያለፈ ምርት እንዳልነበራቸው ተናግረዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅመው ማልማት በመጀመራቸው የተሻለ ምርት እያገኙ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ዘንድሮም ካለሙት ማሳ ጥሩ ውጤት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል። የእርሻ ትራክተር በመጠቀም በኩታ ገጠም እርሻ ሰሊጥ፣ በቆሎ፣ ሩዝ፣ ማሽላና ሌሎች ሰብሎችን በማልማት ከራሳቸው አልፈው ለገበያ እያቀረቡ እንደሚገኙ የጠቀሱት ደግሞ የዲማ ወረዳ አርሶ አደር አቶ ወርቅነህ ይርዳው ናቸው። በዞኑ የአቦቦ ወረዳ የመንደር 13 አርሶ አደር አቶ በለጠ አባተ፤ የተሻሻሉ የግብርና አሠራሮችን በመከተል ሥራ ከጀመሩ ወዲህ ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። በተለይም በክላስተር ተደራጅተው በጋራ ማምረት በመቻላቸው ተጠቃሚነታቸው እየጨመረ መምጣቱን አስረድተዋል። የአኝዋህ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ኝኬው ጊሎ፤ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። አርሶ አደሮቹ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅመው እንዲያመርቱ ዘመናዊ የእርሻ መሣሪያ አቅርቦት መመቻቸቱን ተናግረዋል። በዘንድሮው የምርት ዘመን መጠነኛ የዝናብ መቆራረጥ መከሰቱን የጠቀሱት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ፤ ይህንን ተከትሎ የምርት መቀነስ እንዳያጋጥም በአጭር ጊዜ በሚደርሱ ሰብሎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። በክልሉ የመኸር ወቅት ለማልማት ከታቀደው 180 ሺህ ሄክታር መሬት አብዛኛው በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን ከክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በመሶብ የአንድ ማዕከል ያገኘነው ቀልጣፋ አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ጊዜያችንን ለመቆጠብ አስችሎናል
Aug 14, 2026 47
ሀዋሳ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦ በሃዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል ያገኘነው ቀልጣፋ አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ጊዜያችንን ለመቆጠብ አስችሎናል ሲሉ ተገልጋዮች ገለጹ። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የመሰሉና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፉ አሠራሮች አገልግሎትን የሚያቀላጥፉና የተገልጋይ እንግልትን የሚያስቀሩ የመደመር መንግስት እሳቤ ፍሬዎች ናቸው። አገልግሎቱ አላስፈላጊ ቢሮክራሲን በማስወገድ፣ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ እና የአገልግሎት አሰጣጥ ጊዜን ከቀናት ወደ ደቂቃዎች በማሳነስ የዜጎችን ጊዜ፣ ጉልበትና ገንዘብ እንዲቆጠብ እያደረገ ይገኛል። የሐዋሳው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የሚሰጠው ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር ከዚህ ቀደም የነበረውን የጊዜ ብክነትና እንግልት እየቀነሰ መሆኑን ተገልጋዮች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ደሳለኝ ፋንታ የተባሉ የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ የንግድ ፈቃድ ለማሳደስ ወደ ማዕከሉ መምጣታቸውን ጠቅሰው፤ በ10 ደቂቃ ውስጥ ጉዳያቸውን መጨረሳቸውን ተናግረዋል፡፡ መንግሥት ማዕከሉን ለማስፋፋት የወሰደውን ቁርጠኝነት ያደነቁት ተገልጋዩ፤ ዜጎችም ለውጤታማነቱ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸውም አመልክተዋል፡፡ የማዕከሉ አገልግሎት የተደራጀና ዘመኑን የዋጀ በመሆኑ ከዚህ ቀደም የሚስተዋሉ መጉላላቶች ቀርተው ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላኛዋ ተገልጋይ ወይዘሮ ሰላማዊት ከፈለኝ ናቸው፡፡ ለስም ዝውውርና ለንግድ ፈቃድ እድሳት መምጣታቸውን ጠቅሰው በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልጸዋል፤ የተለያዩ ተቋማት በአንድ ማዕከል ውስጥ መኖራቸው አሠራሩን ቀልጣፋ አድርጎታልም ብለዋል፡፡ አቶ ሸምሱ ተስፉ የተባሉ የማዕከሉ ተገልጋይ በበኩላቸው፤ የማዕከሉ ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር በደቂቃዎች ውስጥ የመጡበትን ጉዳይ ለመፈፀም እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡ ይህም ጊዜ፣ ገንዘብና ጉልበታቸውን እንደቆጠበላቸው ገልጸው፤ መንግሥት ማዕከሉን በማስፋፋት በአገልግሎት ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ የጀመረው ሥራ ውጤታማ መሆኑን መስክረዋል፡፡ መሶብ የተገልጋይን እርካታ ከማሳደግ ባለፈ የሠራተኛውን የሥራ ባህል የቀየረ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በማዕከሉ የሐዋሳ ከተማ መሬት አስተዳደርና ኢንቨስትመንት መምሪያ ቡድን መሪ አዛሪያስ አስማማው ናቸው፡፡ በማዕከሉ የሚሰጠው አገልግሎት የሚፈጸምበትን የጊዜ ገደብ በማሻሻልና ቅድሚያ ማግኘት የሚገባቸውን በመለየት ጭምር የተገልጋይ እርካታን ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ የሐዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ኤርሚያስ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ የሚሰጠው ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር በአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፍ ለሚታዩ ችግሮች መፍትሔን ያመጣ ነው ብለዋል፡፡ ባሳለፍነው ግንቦት ወር መጨረሻ ሥራ በጀመረው የሐዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 13 የሚደርሱ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት 57 አገልግሎቶችን እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በማዕከሉ እስካሁን ከ37 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን ገልጸው፤ ተገልጋይ ተኮር የሆነው አሰራር የተገልጋይ እርካታን እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል፡፡
የሀገር ሉዓላዊነትንና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቅ ዘመናዊ ሰራዊት ለማደራጀት ቴክኖሎጂ ወሳኝ ነው-ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Aug 12, 2026 207
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፦የሀገር ሉዓላዊነትንና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቅ ዘመናዊ ሰራዊት ለማደራጀት ቴክኖሎጂ ወሳኝ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ፡፡ የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የተደራጀ ዘመናዊ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለመገንባት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በስምምነቱ ወቅት እንደገለጹት፥ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩቱ መቋቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ የሀገርን ሉዓላዊነት እና ብሔራዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ ዘመናዊ ሠራዊት ለማደራጀት በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ መታገዝ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የኤ.አይ ቴክኖሎጂ ለመከላከያ ኃይል በተለይም በአየር፣በምድር እና በሳይበር አቅም ግንባታ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ም የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ለመደገፍ ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑንም ገልጸዋል። ሁለቱ ተቋማት በሎጂስቲክስ፣ በስልጠና፣ በሳይበር ደህንነት፣ በመከላከያ ሰራዊት ጤና አጠባበቅ፣እንዲሁም በአየር ኃይል እና በኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር ዘርፎች በኤ.አይ በመታገዝ የሠራዊቱን አቅም ማሳደግ የሚያስችሉ አበይት ጉዳዮችን ላይ መወያየታቸውን ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዞ አንዱ መገለጫ -መሶብ
Aug 12, 2026 310
(በሙሴ መለሰ) የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች መመላለስ፣ የወረቀት ክምርና ረጅም ሰልፍ የኢትዮጵያውያን የቆየ የዕለት ተዕለት ፈተና ነበር። ይህንን የዜጎች እንግልት በዘላቂነት ለመቅረፍ እና አሰራርን ለማዘመን ታስቦ የተመሠረተው መሶብ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል። የተቀናጀው የ"አዲስ መሶብ" ሱፐር አፕ (Super App) ዲጂታል መድረክ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ወደ ሙሉ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። የመሶብ ዋና ዓላማ ተበታትነው የነበሩ ልዩ ልዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ አጋዥነት በአንድ ጣሪያ ስር ማገናኘት ነው። ዜጎች ጊዜና ገንዘባቸውን ሳይባክኑ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ፣ የሰዎችን ቀጥተኛ ንክኪ በመቀነስ ሙስናና ብልሹ አሰራርን መዋጋት፣ እንዲሁም ግልጽነትን ማስፈን የተቋሙ መሠረታዊ ምሰሶዎች ናቸው። በረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ደግሞ እያንዳንዱ ዜጋ በብሔራዊ የፋይዳ (Fayda) መታወቂያው ብቻ በመጠቀም ሁሉንም የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ አካውንት እንዲያገኝ ማድረግ እና ሥርዓቱን ለአፍሪካ ሀገራት እንደ መሪ ተሞክሮ ማቅረብን ያለመ ነው። ይህ የዲጂታል መድረክ እና አጠቃላይ የቴክኖሎጂ ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሀገር በቀል እውቀት የበለጸገ ሲሆን፣ ጥቅም ላይ የዋሉት የሶፍትዌር ቴክኖሎጂዎች ለሁሉም ክፍት የሆነ (Open-source) መሆናቸው ተቋሙን ከከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ አድኖታል። በማዕከላቱ ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች ጥብቅ የሆነ የምልመላ ፈተና እና ልዩ ስልጠናዎችን አልፈው የሚገቡ በመሆናቸው የአገልግሎት ጥራቱ ከብልሹ አሰራር የፀዳ እንዲሆን አስችሏል። መጀመሪያ ላይ በ12 ተቋማትና በ41 አገልግሎቶች ብቻ የተጀመረው ይህ ዘመናዊ አሰራር፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እያሳየ ባለው ፈጣን እድገት በአሁኑ ወቅት የትስስር አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችሏል። አሁን ባለው ተጨባጭ ቁመና መሶብ 27 ዋና ዋና የመንግሥት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መስመር ማገናኘት የቻለ ሲሆን፣ እነዚህ ተቋማት በአንድ ላይ በመቀናጀት ከ288 በላይ የተለያዩ ዲጂታል አገልግሎቶችን በጥራትና በፍጥነት እያቀረቡ ይገኛሉ። ተገልጋዮች እንደ ፓስፖርት፣ ውክልና፣ የንግድ ፈቃድ እና የሰነዶች ማረጋገጫ ያሉ ወሳኝ ጉዳዮቻቸውን በአንድ ማዕከል ወይም በሞባይል መተግበሪያቸው ማከናወን ይችላሉ። ይህንን ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ100 በላይ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ማዕከላት የተቋቋሙ ሲሆን፣ እስካሁንም ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በማስተናገድ የአገልግሎት እርካታውን በፌዴራል ደረጃ ወደ ከ98 በመቶ በላይ ማድረስ ተችሏል። በቅርብ ቀናት ውስጥ የወጡ አዳዲስ ወቅታዊ መረጃዎች ደግሞ ተቋሙ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ እና ተለዋዋጭ እያደረገው መሆኑን ያሳያሉ። በቀን የሥራ ሰዓት መስተናገድ ለማይችሉ ሠራተኞችና ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ከተለመደው የሥራ ሰዓት ውጭ የምሽት አገልግሎት (Night Service) በይፋ ተጀምሯል። ከዚህ በተጨማሪ ወደ ማህበረሰቡ በቀጥታ በመሄድ አገልግሎት የሚሰጡት እና የራሳቸውን ኃይል በከፊል ከፀሐይ ብርሃን የሚያመነጩት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ አውቶቡሶች (Mobile Mesob Bus) በተለይ ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች የቤት ለቤት አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። የጤናው ዘርፍ አገልግሎቶችንም ለማካተት ከቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ጋር አዲስ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ ወደ ሀገር ለሚገቡ ባለሃብቶችና ዳያስፖራዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በቦሌ ዓለም አቀፍ አየውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ማዕከል እየተገነባ ይገኛል። በአዲስ አበባ ከተማም ከ480 በላይ የአገልግሎት መስኮቶች የሚኖሩት አንድ ግዙፍ ማዕከላዊ የኮምፕሌክስ ሕንፃ ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ ነው። “ዩኒፋይድ መሶብ” የተሰኘው የኦንላይን መድረክ ዜጎች በሞባይል ስልካቸው የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችል ሥርዓትም ተግባራዊ ሆኗል። በአሁኑ ወቅት መሶብ ከሀገር ውስጥ አልፎ ዓለም አቀፍ ትኩረትን እየሳበ ይገኛል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቤኒን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን ማዕከሉን በይፋ የጎበኙ ሲሆን፣ መሶብ ለአፍሪካ ሀገራት በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመንግሥት አገልግሎት ሥርዓት ለመገንባት እንደ ትልቅ የምርጥ ተሞክሮ ማሳያ እየተወሰደ ነው። በቀጣይም ከጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ጋር በዲጂታል አገልግሎት ዙሪያ የጋራ ትስስር በመፍጠር የአህጉር አቀፍ የዲጂታል ሥርዓት የመገንባት ስትራቴጂ ተነድፎ እየተሰራ ይገኛል። በአጠቃላይ መሶብ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን እና የሕዝብን እንግልት በመቀነስ ረገድ ውጤታማነቱን በተግባር ያረጋገጠ ስኬታማ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማሳያ ነው።
ማእከሉ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት እያገዘ ነው
Aug 12, 2026 191
ባህር ዳር ፤ነሀሴ 6/2018 (ኢዜአ)፡ -የባህር ዳር መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። መንግስት መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎትን በማስፋፋት ዜጎች ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋለውን የመልካም አስተዳደር ችግር እየፈታ ይገኛል። እንዲሁም ዜጎች በአንድ ቦታ የተቀናጀ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ከአላስፈላጊ ወጭና እንግልት ከመታደግ ባለፈ ብልሹ አሰራርን እያስቀረም ይገኛል። ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የረዳቸው መሆኑን ተናግረዋል ። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ አብርሃም ያረጋል እንደገለጹት፣ የባህር ዳር መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከተማዋን የሚመጥን አግልግሎት እየሰጠ ነው። መንጃ ፈቃድ ለማደስ ወደ ማእከሉ መምጣታቸውን ጠቁመው ቀደም ሲል ከሁለት ቀን በላይ ይወስድ የነበረው እድሳቱ በማእከሉ ከ30 ደቂቃ ባነሰ ጊዜ ውስጥ አገልግሎቱን ማግኘታቸውን ተናግረዋል ። የሰራተኞቹም መልካም መስተንግዶ እንዲሁም ግልጽነትና ፍትሃዊነት የሰፈነበት አሰራር አስደሳች መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ ብልሹ አሰራር እንዲወገድ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቁመዋል። ሌላዋ የከተማው ነዋሪ ውባየሁ ጥጋቡ በበኩላቸው የወሳኝ ኩነት መረጃዎችን ለማስፈጸም ከዚህ ቀደም ሁለት ቦታ መሄድ ይጠይቅ እንደነበር አስታውሰው በማእከሉ በሚሰጠው የተቀናጀ አገልግሎት ችግሩ መፈታቱን ተናግረዋል ። በማእከሉ ምንም አይነት መጉላላት ሳይገጥማቸው ፈጣንና ባጭር ጊዜ ውስጥ የተሳለጠ አገልግሎት ማግኘታቸውን አስረድተዋል። የባህር ዳር መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ማስረሻ ፈንታ በማእከሉ 14 ተቋማት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። በተቋማቱ 91 የተለያዩ አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን አመልክተዋል። በማእከሉ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በሚሰጠው አገልግሎት በየቀኑ እስከ 400 የሚደርሱ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም መፈጠሩን ተናግረዋል። ማእከሉ ስራ ከጀመረበት ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ከ75 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተገልጋዮች አገልግሎት መስጠቱ ተመላክቷል ።
ስፖርት
የ2019 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መስከረም 7 ይጀመራል
Aug 13, 2026 137
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም እንደሚጀመር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። የሴቶች ፕሪምየር ሊግ ክለቦች ለአዲሱ የውድድር ዓመት ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲያደርጉ፤ የውድድሩን ፎርማት በተመለከተ በደርሶ መልስ ጨዋታ ማድረግ የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር በቅርብ ጊዜ ውስጥ ክለቦችን በመጥራት ውይይት እንደሚካሄድም ገልጿል፡፡
ኢትዮጵያን በሶስት የአፍሪካ ዋንጫዎች የወከሉት ታዋቂው የብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፍስሐ ወልደአማኑኤል ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
Aug 13, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ከታዩ ታላላቅ ተጫዋቾች አንዱ የሆኑት ፍስሐ ወልደአማኑኤል ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። "ኳስ ፊደሉ" እና "ጠመንጃው" በሚሉ ቅጽል ስሞች የሚታወቁት አቶ ፍስሐ፣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ እና ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጨዋታ ዘመናቸው ከፍተኛ አገልግሎት ሰጥተዋል። ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋርም የኢትዮጵያ ሻምፒዮና እና ዋንጫዎችን አሸንፈዋል። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይም የብሔራዊ ቡድኑን ማልያ ለብሰው ተሰልፈዋል። ለከፍተኛ ትምህርት ወደ አሜሪካ አምርተው ኑሯቸውን እዚያው ያደረጉት አቶ ፍስሐ፣ ለሀገሪቱ ክለቦች ከመጫወታቸው በተጨማሪ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን (ESFNA) መስራች አባል እና ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በህልፈታቸው የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ፣ ለቤተሰብ፣ ለወዳጅ ዘመድ እና ለስፖርት ቤተሰቡ መጽናናትን ተመኝቷል።
ፒኤስጂ የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ባለቤት ሆነ
Aug 13, 2026 256
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ መርሐ ግብር ፒኤስጂ አስቶንቪላን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በኦስትሪያ በሚገኘው ሬድ ቡል አሬና በተካሄደው ጨዋታ ክቪቻ ክቫራትስኬሊያ እና ዴዚሬ ዱዌ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። የ17 ዓመቱ ታዳጊ ብሪያን ማጆ የአስቶንቪላ ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጨዋታው አዝናኝ እና በርካታ የግብ እድሎች የተፈጠሩበት ነበር። ፒኤስጂ የአውሮፓ አሸናፊ አሸናፊዎች ዋንጫ አንስቷል። በሉሲስ ኤነሪኬ የሚመራው ፒኤስጂ ባለፈው የውድድር ዓመትም ላይ ቶተንሃምን በተመሳሳይ በመለያ ምት አሸንፎ የዋንጫው ባለቤት እንደነበር የሚታወስ ነው። የፈረንሳዩ ክለብ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ዋንጫ አግኝቷል። አስቶንቪላ ዋንጫውን በብቸኝነት ያነሳው እ.ኤ.አ በ1982 ባርሴሎናን በማሸነፍ ነበር። ከ44 ዓመት በኋላ ዋንጫውን የማንሳት ህልሙ አልተሳካም። የ34 ዓመቱን ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታን ጨዋታውን በዋና ዳኝነት መርቷል። ይህም በውድድሩ የ51 ዓመታት ታሪክ ውስጥ የአሸናፊዎች አሸናፊ ጨዋታን የመሩ የመጀመሪያው የአውሮፓ ዜግነት የሌላቸው ዳኛ አድርጓቸዋል። የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ የክለቦች ውድድር አሸናፊዎችን የሚያገናኝ የዓመቱ ማጠቃለያና አዲስ የውድድር ዘመን መክፈቻ መርሐ ግብር ነው። የጨዋታው አሸናፊው ፒኤስጂ የአምስት ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ሽልማት የሚያገኝ ሲሆን፥ ተሸናፊው አስቶንቪላ ደግሞ አራት ሚሊዮን ዩሮ ወደ ካዝናው ያስገባል።
ፒኤስጂ ከአስቶንቪላ፤ የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ፍልሚያ
Aug 12, 2026 211
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ መርሐ ግብር ዛሬ በፒኤስጂ እና አስቶንቪላ መካከል ይደረጋል። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ ኦስትሪያ በሚገኘው ሬድ ቡል አሬና ይካሄዳል። የፈረንሳዩ ፒኤስጂ ለዚህ ጨዋታ የበቃው በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ላይ አርሰናልን በመለያ ምት አሸንፎ ዋንጫውን በማንሳቱ ነው። በሉሲስ ኤነሪኬ የሚመራው ፒኤስጂ ባለፈው የውድድር ዓመትም ላይ ቶተንሃምን በተመሳሳይ በመለያ ምት አሸንፎ የዋንጫው ባለቤት እንደነበር የሚታወስ ነው። በሌላ በኩል አስቶን ቪላ በአሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ መሪነት በዩሮፓ ሊግ ፍጻሜ የጀርመኑን ፍራይበርግ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለዛሬው ጨዋታ በቅቷል። በታሪክ አስቶን ቪላ እ.ኤ.አ በ1982 ባርሴሎናን አሸንፎ ዋንጫውን አንዴ ጊዜ አንስቷል። ፒኤስጂ እና አስቶን ቪላ ከዚህ ቀደም በአውሮፓ መድረክ የተገናኙት እ.አ.አ 2024/25 የሻምፒዮንስ ሊግ ሩብ ፍጻሜ ላይ ብቻ ነበር። በወቅቱ ፒኤስጂ በሜዳው 3 ለ 1 ሲያሸንፍ፥ አስቶን ቪላ በቪላ ፓርክ የ3 ለ 2 ድል አስመዝግቧል። በድምር ውጤት ፒኤስጂ 5 ለ 4 በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜ ያለፈ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ መሆን ችሏል። ይህንን ጨዋታ ይበልጥ ልዩ የሚያደርገው በዳኝነት ረገድ የሚመዘገበው አዲስ ታሪክ ነው። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (ዩኤፋ) ጨዋታውን በዋና ዳኝነት እንዲመሩ የ34 ዓመቱን ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታንን መርጧል። ይህም በውድድሩ የ51 ዓመታት ታሪክ ውስጥ የአሸናፊዎች አሸናፊ ጨዋታን የመሩ የመጀመሪያው የአውሮፓ ዜግነት የሌላቸው ዳኛ ያደርጋቸዋል። የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ የክለቦች ውድድር አሸናፊዎችን የሚያገናኝ የዓመቱ ማጠቃለያና አዲስ የውድድር ዘመን መክፈቻ መርሐ ግብር ነው። ጨዋታው መደበኛው 90 ደቂቃ በአቻ ውጤት ከተጠናቀቀ፥ ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ ሳይሄድ በቀጥታ ወደ መለያ ምት ያመራል። የጨዋታው አሸናፊው ቡድን የአምስት ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ሽልማት ሲያገኝ፥ ተሸናፊው ደግሞ አራት ሚሊዮን ዩሮ ወደ ካዝናው ያስገባል። የውድድሩ ስኬታማ ክለብ ሪያል ማድሪድ ሲሆን ስድስት ጊዜ ዋንጫውን አንስቷል። ባርሴሎና እና ኤሲ ሚላን በተመሳሳይ በአምስት ዋንጫዎች ይከተላሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያስተናግዳሉ
Aug 13, 2026 136
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያስተናግዱ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ በስፋት ያስተናግዳሉ። በደቡብ ምዕራብ፤ ምዕራብ፤ ሰሜን ምዕራብ፤ ሰሜን፤ መካከለኛው፤ ምሥራቅ እና ሰሜን ምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚኖራቸው በመግለጫው ተመላክቷል። በምዕራብ፤ ሰሜን ምዕራብ ፤ ደቡብ ምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች እርጥበታማ የአየር ሁኔታም ከመጠናከሩ ጋር በተገናኘ በተጠቀሱት አካባቢዎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያስተናግዱ ይጠበቃል። በሰሜን ምሥራቅ፤ ምሥራቅ እና ደቡብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ደግሞ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል። በተመሳሳይ ሁኔታ በሰሜን ምዕራብ፤ ደቡብ ምዕራብ፤ መካከለኛው፤ ምዕራብ እና ሰሜን ምሥራቅ የሀገሪቱን አካባቢዎች ላይ አልፎ አልፎ ከሚከሰቱት የአየር ሁኔታ ክስተቶች ጋር ተያይዞ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል። ኢንስቲትዩቱ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ፤ የመኸር ሰብል አብቃይ፤ አርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረውን እርጥበት ለግብርና ስራዎቻቸው ውጤታማነት በአግባቡ እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርቧል። በዚህም መሰረት የአጭር ጊዜ የመኸር ሰብሎችን በመዝራት ፣የሰብል በሽታንና አረምን አስቀድሞ በመከላከል ፣ተዳፋታማ ማሳዎች ላይ የተዘጉ የማፋሰሻና የማንጣፈፊያ ቦዮችን በማስተካከል የእርጥበት ሁኔታዎን ወደ ውጤት ሊያውሉ እንደሚገባ አመላክቷል። በተጨማሪም እርጥበት አጠር አካባቢዎች የዝናብ ውሀን ማሰባሰብና ማጠራቀም፣ የመሬት መንሸራተትና የአፈር መሸርሸር መከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን፤ የማዳበሪያ አጠቃቀምን በትክክለኛው ሰዓት ጠቀም ተገቢ መሆኑንም ገልጿል። ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው እርጥበት የሚያስተናግዱ አካባቢዎችም የሚገኘውን እርጥበት ለእርሻ በቂ መሆኑን በማረጋገጥ የአጭር ጊዜ የመኸር ሰብሎችን መዝራት ፣የአፈር ውስጥ የትነት መጠንን ለመቀነስ የሚያስችሉ አሰራሮችን መዘርጋት እና ለእንስሳት የግጦሽ ሳርን በአግባቡ መጠበቅና ማዘጋጀት ሊወሰዱአቸው ከሚገቡ ጥንቃቄዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸው ተጠቁሟል። በመሆኑም የሚመለከታቸው አካላቶች የእርጥበት ሁኔታው በውሀ አካላት ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ በመገንዘብ የጎርፍ አደጋ የመሬት መንሸራተት እንዲሁም የደራሽ ወንዝ ሙላት እና ሌሎች ተያያዥ የሆኑ የተፈጥሮ አደጋዎችን መከላከል የሚስችሉ ተግባራትን እንዲያከናውኑ ምክረ ሀሳብ አቅርቧል።
ዩኒቨርሲቲው በብዝሃ ህይወት እና ዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ረገድ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች በምርምር እንዲፈቱ እያገዘ ነው
Aug 11, 2026 354
ሮቤ፤ ነሐሴ 5/2018(ኢዜአ)፡- የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በብዝሃ ህይወት እና ዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃና እንክብካቤ ረገድ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች በምርምር ተለይተው እንዲፈቱ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ከኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት የጎባ ቅርንጫፍ ጋር በመቀናጀት "ተስፋን እንትከል'' በሚል መሪ ሀሳብ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ዛሬ አካሄደዋል። የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬት በየጊዜው ከሚያደርገው ተሳትፎ በተጓዳኝ በዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ረገድ ሳይንሳዊ ምርምር እያካሄደ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው በተለይም በባሌ አካባቢ የሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን በሳይንሳዊ ምርምር የማገዝ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጾዋል። በዩኒቨርሲቲው የሚካሄዱት ምርምሮች፣ ከችግኝ ተከላ ጋር ተያይዘው በአየር ንብረትና በአካባቢ ላይ የሚደርሱ ችግሮችን በጥናት ለመለየትና መፍትሔ ለመስጠት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት የጎባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በንቲ ኦፍገሃ በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከዩኒቨርሲቲው ጋር በተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ዙሪያ ባለፉት ሦስት ዓመታት የተሰሩት ሥራዎች የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ገልጸው፤ በተለይም የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ በመደረጋቸው ጠፍተው የነበሩ የዱር እንስሳትና ምንጮች እየጎለበቱ መምጣታቸውን ጠቁመዋል። በችግኝ ተከላው ከተሳተፉ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት መካከል መምህር ኡመር መሐመድኑር፣ በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ እንደ ዜጋ በየዓመቱ ከመሳተፍ ባሻገር ችግኞቹ ፀድቀው ለውጤት እንዲበቁም የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ሥራው የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ለኢኮኖሚ ዕድገት መፍትሄ በሚሆን አግባብ መከናወን እንደሚገባውም እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በጎባ ክፍለ ከተማ ''ስራክ ጥብቅ ደን'' አካባቢ በተካሄደው መርሐ ግብር የደን፣ የመጠለያ፣ የእንስሳት መኖና ሌሎች ችግኞች መተከላቸውን ለማወቅ ተችሏል።
የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተከላ፣ክትትልና የፅድቀት መጠን በጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ እየተረጋገጠ ነው
Aug 10, 2026 311
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፦የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተከላ፣ ክትትልና የፅድቀት መጠን በጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ እየተረጋገጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በኢንስቲትዩቱ የካርታ ስራ መሪ ስራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ካሳሁን ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሳይንሳዊ የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ፣በጂፒኤስ (GPS) ልኬትና በሳተላይት ምስል ትንተና መደገፍ መጀመሩ በመረጃዎች ጥራትና በውጤታማነት በኩል ከፍተኛ ለውጥ አምጥቷል። የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ በዋናነት የመረጃዎችን የት፣እንዴት እና መቼ የሚሉ ሶስት መሰረታዊ ጥያቄዎች በትክክል መመለስ እንደሚረዳ ተናግረዋል። እንደ አቶ ቴዎድሮስ ማብራሪያ፣በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ችግኝ የሚተከልባቸው ቦታዎች በጂፒኤስ ንባብ አማካኝነት መጋጠሚያቸው ተለይቶ የተመዘገቡና ያልተመዘገቡ ተብለው ይከፈላሉ። በቅርቡ በተካሄደው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ከ291 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ሙሉ በሙሉ በጂፒኤስ ተለክቶና የቦታ ስፋቱ ተሰልቶ መደራጀቱን ጠቁመዋል። ይህ አሰራር ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ የመረጃ መደጋገሞችንና የመረጃዎች መሳሳትን ሙሉ በሙሉ ማስቀረቱን ገልፀዋል። አሁን ተግባራዊ በተደረገው አሰራር መረጃው ቢሮ እንደደረሰ በሳተላይት ምስል እንደሚረጋገጥ ጠቁመው፤ በተመረጡ ቦታዎች ላይ ባለሙያዎች በአካል በመገኘት የማረጋገጥ ስራ እንዲሰሩ ተደርጓል ብለዋል። ችግኝ መትከል ብቻውን ግብ አለመሆኑን በመግለጽ፣የተተከሉ ችግኞች ማደጋቸውንና የአካባቢውን አረንጓዴነት መለወጣቸውን ለመከታተል የርቀት ቴክኖሎጂ (Remote Sensing) ትንተና ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። ባለሙያዎች የደረቅ ወቅት የሳተላይት ምስሎችን በመጠቀም የመሬት ሽፋኑን (የከተማ፣ የእርሻ፣ የወንዝ እና የደን) የሪፍሌክታንስ (Reflectance) ዋጋ በመተንተን ትክክለኛውን የደን ሽፋን እንዲለዩ ይደረጋል ብለዋል። በዚህ ሳይንሳዊ መንገድ በተካሄደው ዳሰሳና በመስክ ማረጋገጫ ስራ፣ ቀደም ሲል 17 በመቶ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን በአሁኑ ወቅት ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማደጉ መረጋገጡን ገልጸዋል። ይህ ትልቅ ስኬት የተገኘው ህብረተሰቡ ባለፉት ስምንት ዓመታት ባደረገው ያልተቋረጠ ጥረትና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በተከናወኑ ስራዎች መሆኑንም አመላክተዋል። በአሁኑ ወቅት ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጃቸውን የደን፣ የሰብልና የከተማ መረጃ ክትትልን ጨምሮ 10 ማዕከላትን በመጠቀም መረጃዎችን ለውሳኔ ሰጪዎችና ለግብርና ሚኒስቴር ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 636
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 629
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች። ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 908
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1411
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር!
Aug 9, 2026 640
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር! በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን ) የገጠሩ ማህበረሰብ የጨለማ ኑሮ የተፈረደበት ይመስል ኑሮውን ማሻሻል ሳይችል እልፍ ዓመታት ተቆጥረዋል፤ ለዘመናት መብራትና ውኃ ለማግኘትና ከቴክኖሎጂ ጋር ተቀራርቦ ለመኖር ወደ ከተማ መሰደድ ብቸኛው አማራጭም ነበር። የከተሜው ዋልታ የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት የሚወሰንበት የአራሹ ገበሬ የኑሮ ደረጃ ባህላዊውን የአኗኗር ዘዬ ባለመልቀቁ ደስተኛ ጊዜ የሚያሳልፍበት ሂደት አድካሚ እንደሚሆን ግልጽ ነው። የገጠሬው የተበታተነ የአኗኗር ሥርዓትም ለገጠሬው አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፤ የእዚህን የህብረተሰብ ክፍል ምርቱን እንጂ ኑሮውን የጠየቀ አልነበረም ቢባል ግነት አይሆንም። ቀደም ሲል በነበሩ መንግስታት ከተማን እንጂ ገጠርን ማዘመን የሚያስብ ስለመኖሩ ያጠራጥራል፤ ይህም በሀገሪቱ ለኢፍትሐዊ ዕድገት የራሱን ተጽዕኖ ሲያሳደር ቆይቷል። የመደመር መንግሥት ግን ይህን ቀይሮታል። ሀገር የመምራት ኃላፊነት ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ በከተማና በገጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ በዜጎች የኑሮ ሥርዓት ላይ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርጎ እየሰራ ነው ከተሜነት ብቻውን አድጎ የገጠሩ ማኅበረሰብ በቀድሞ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሆነ የተሟላ ዕድገት ማምጣት አይቻልም የሚል ጽኑ እምነት አለው። በእዚህም ከተማና ገጠርን ለማቀራረብ በገጠር ትራንስፎርሜሽንን የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ቀርጾ መተግበር ከጀመረ ከራርሟል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን አንዱ አካል የሆነው የገጠር ሞዴል መንደር በአርሶ አደሮች ዘንድ የሚጨበጥ ተስፋን ይዘው ከመጡ ኢኒሼቲቮች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። ከተስፋ ተሻግረው በዚህ ሞዴል መንደር የነዋሪነት ዕድልን ያገኙት ደግሞ ብርሃን አይተዋል፤ የትናት አኗኗራቸውን የቀየረ አዲስ ዛሬን በእጃቸው አድርገዋል፤ ነገን አልቀው መመልከት የግብርና ተግባራቸው አንዱ አካል ሆኗል። በአዲሱ መንደራቸው ዛሬ የሚያፈስ ቤት የለም፣ የእንስሳት ቆሻሻ ሽታ በአፍንጫቸው አይገባም፣ በሚቆረቁር እንጨት ወይም መደብ ላይ አይቀመጡም፤ የከተሜው መዘነጫ ሶፋ በሳሎናቸው ተከስቷል። ጓሮዎቻቸው ሁሉ ሙሉ እንደሆኑ አፍ አውጥተው የሚያወሩ ናቸው። በዚህ ቆስጣ፤ በዛ በኩል ጎመንና ቀይስር፤ ዘውር ሲሉ ደግሞ ከአስር የሚልቁ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፤ በአንድ ክፍል ደግሞ እናት ላም ከጥጃዋ ጋራ፣ የእንቁላል ዶሮ ከሥጋ ዶሮ ጋር ሁሉንም በአንድ ጊቢ ውስጥ ያገኛሉ። ምን ይሄ ብቻ አቮካዶ እና ፓፓያ፣ ሙዝና እንሰት፣ በርበሬና ሽንኩርት ሳይቀር ለተትረፈረፈ የአርሶ አደር ማዕድና ገበያ ራሳቸውን አዘጋጅተዋል። አርሶ አደር ኃይሉ ሞትንሞስ በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ ናቸው። እርሳቸው "መንግስት ጨለማችንን ገፎ ብርሃን አሳየን" ሲሉ በጠንካራ ቃላት የገጠር ሞዴል መንደር ፕሮጀክት ያመጣላቸውን በጎ ነገር ይገልጻሉ። እውነት ነው ያላዩትን ብዙ ነገር አሳይቷቸዋል። ያም ብርሃን ቤት ውስጥ የሚበራ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው፣ በነገ ተስፋቸውና በኢኮኖሚያቸው ላይ የፈነጠቀ ብርሃን ነው። ዛሬ ያሉበትን ህይወትም "ለእኔ አዲስ ነገር ነው። አይቼው አላውቅም፤ መቼም በራሴ ሀሳብ አላደርገውም ነበር።" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግስት አበራልኝ ያልኩት በእጄ ያለኝን ያላየሁትን ዕድል ስላሳየኝ ነው በማለትም ሀሳባቸውን ይቀጥላሉ። እኛ ሀብት አለን፤ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም። ይልቁንም የምናባክነው ይበዛል በማለትም የቀደመ ሕይወታቸውን እያሰቡ ይቆጫሉ። አሁን ግን ብዙ ተገነዘብኩ የሚያስብል የመደመር መንግስት በመኖሩ አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። እርግጥ ነው የገጠር ሞዴል መንደር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ነው። ለአብነትም የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ማንሳት ይቻላል። የተሠሩ ሞዴል መንደሮች በመጀመሪያ የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ የመሆን ዕድል ገጥሟቸዋል። በመቀጠል ንጽሕናው ያልተረጋገጠ የመጠጥ ውኃ ወንዝ ወርዶ ከመቅዳት ተቆጥበው በመንደራቸው የተገነባውን የከረሰ ምንድር ውሃ ከቧንቧ ቀድተው መጠጣት አስችሏቸዋል። በእሳት እና ኩራዝ ጭስ ሲሰቃዩ የነበሩ ዓይኖቻቸው ዛሬ ከሶላር ቴክኖሎጂ የመነጨ ብርሃን ማየት ጀምረዋል። ብርሃን ብቻ አይደለም ለወትሮ ለገበያ ወደ ከተማ ብቻ ሲወጡ ይመለከቱ የነበረውን ቴሌቪዥን ዛሬ በቤታቸው አስገብተው የመረጃና የመዝናኛ ዓለምን ተቀላቅለዋል። አርሶ አደሮቹ ቴሌቭዥንን ከመዝናኛነት ይበልጥ ለመረጃ እንደሚጠቀሙት ያነሳሉ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በዜና ተከታትሎ መረዳት፣ የገበያ ሁኔታን ማወቅ፣ የግብርና ሥራ ተሞክሮን መቅሰምና የአየር ንብረት ሁኔታን ጨምሮ ለሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙት ከቴሎቪዥን መስኮት እንደሆነ ይናገራሉ። በጓሯቸው የተትረፈረፈ የሌማት ትሩፋት ምርት መሰብሰብ የሚያስችላቸው ምቹ ሁኔታ ደግሞ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው። በተለይ መንግስት በጓሯቸው ጥምር እርሻ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የነገ ኢኮኖሚያቸውን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ ነው። ከተማን መናፈቅን ያስቀረው የገጠር ሞዴል መንደር ያኔ ከጅምሩ አመኔታን አላገኘም። የቦታና የአካባቢ ቁሳቁስ ለማቅረብ ዝግጁ እስካለመሆን የደረሱ አርሶ አደሮችም ነበሩ። በወቅቱ ጉዳዩን እንደፌዝ አዩት። ዛሬ ግን ውጤቱን በአግራሞት በዐይናቸው ተመለከቱ። የተናገረውን የሚከውን፤ የጀመረውን የሚጨርስ የመደመር መንግሥትን ተጨባጭ ስራዎች በማረጋገጥ እንደ ትንግርት ቆጠሩ። ዛሬ በየአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በቁጭት ተሞልተው መንደራቸውን ወደዚህ የሞዴል መንደር እሳቤ ለመቀየር ተነሳስተዋል። የጌሊት ቀበሌ አርሶ አደሮቹ መኮንን አርዶ እና ነጻነት ተስፋሁን ለዚህ ተጠቃሾች ናቸው። ያዩትን ተሞክሮ በራስ አቅም በመንደራቸው ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ከተማ ሄደን የምናወጣውን ወጪና የምናባክነውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት እዚሁ መዝናናት የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል። "ይህ ዕድል ለእኛ ለአርሶ አደሮች በታሪክ የሚነገር ትልቅ አጋጣሚ ነውም" ይላሉ። በጤዛ እየራስን እንጓዝበት የነበረው መንገዳችን ዛሬ ሰፍቷል። ተሽከርካሪ በደጃችን ስለሚያልፍም ምቹ ዕድልን ይዞልን መጥቷል። ይህን ጅምር ተግባር ወደ ላቀ ውጤት ማሸጋገር የእኛ ድርሻ ነውና ጠንክረን እንሠራለንም ብለዋል። ይህን ዕድል ወደ ትልቅ አቅም ለመቀየር መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ የሸሸቃ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር አልዓዛር ዘርክናንስ ናቸው። የዶሮና የከበት እርባታን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ ሥራን ከመደበኛው የእርሻ ሥራ ጋር አስተሳስረው በመሥራት ከቤተሰብ ፍጆታ ተርፎ ለገበያ የሚበቃ ምርት ለማምረት እየተዘጋጁ ነው። ይህም የገቢ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ልጆቻቸው ወተትና የወተት ተዋጽኦ በቤታቸው እንዲያገኙ ያደርጋል። ማር፣ እንቁላል እና ሥጋ እንዳያምራቸው የሚያደርግ ትልቅ ኢኒሼቲቭም ነው። አንዱ ቢጎድል በሌላው እየሞሉ የሚኖሩበትን የሥራ መስክ አጠናክረው ለውጤት አብቅተው ለተሻለ ለውጥ እንደሚሠሩ አክለዋል። የአርሶ አደር እናቶች ዘምቢል ይዘው አትክልትና ፍራፍሬ ሸመታ ወደ ገበያ ማቅናት የለባቸውም። ይልቁንም ከጎሮቸው ወደ ገበያ ይዞ መውጣት የኑሮ ዘዬያቸው ወግ ነው። ወይዘሮ መሠረት ማሞ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ያልለመዱትን አዲስ ሕይወት ከአዲስ ተስፋ ጋር መጀመራቸውን ከሚናገሩት መካከል ናቸው። ትናንት ኩሽናቸው፣ መኝታቸው እንዲሁም የከብትና የዶሮ ማደሪያ በአንድ ቤት ወስጥ የተወሰነ እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን ሽንት ቤትና መታጠቢያ ቤት ሳይቀር ለየብቻ የራሱ የሆነ ቤት ተገንብቶ ጽዳቱ የተጠበቀ ኑሮ መኖር ጀምረዋል። ቤታቸው ሲገቡና ሲወጡ ለዓይን ማራኪ፤ ለመቀመጥ ምቹ፤ ለመተኛትም ንጹህና ወገብ የሚያሳርፍ ሆኖ አግኝተዋል። እናም በዚህ እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። "መንግስት እንደ አባት ጎዶሏችንን ሞልቷል" ሲሉም ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ የአርሶ አደሮችን ሕይወት ብሩህ ያደረገው የገጠር ሞዴል መንደር ኢኒሼቲቭ በመላው ሀገሪቱ በመስፋፋት ላይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 16 ሞዴል መንደሮች በ16 ወረዳዎች ተገንብተዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ኢኒሺዬቲቩ የአርሶ አደር ኑሮ ዘዬን ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ጋር ለማቆራኘት ያስቻለ ነው። የተሻለ መኖሪያ ቤት ኖሮት በጓሮው የሚበላ ነገር ካጣ ሕይወቱ ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም። ይህም በመሆኑ ቤቶቹን ከእያንዳንዱ የግብርና ልማት ዘርፎች ጋር በማጣመር እንዲገነቡ የተደረገው። ይህም የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ስትራቴጂን የሚያጠናክርና ገበያን የማረጋጋት ዓላማን የያዘ ጭምር ነው። በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ የተገኘው መልካም ውጤት በቀጣይ በሁሉም ወረዳዎች የሚስፋፋ ሲሆን በዞን እና ወረዳ መዋቅሮች ድጋፍና ክትትል በቀበሌ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አንስተዋል። ይህ ኢኒሼቲቭ የሀገራዊ ብልጽግና ጉዞ አንዱ አቅም ነው። የተደመረ የማኅበረሰብ ብልጽግና ሀገርን ከፍ ያለ የዕድገት ማማ ላይ ያስቀምጣታል። እነሆ የክልሉ አርሶ አደሮች የአካባቢያቸውን ጸጋ ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ የሚቀይሩበት መስክ በሞዴል መንደር ምክንያት እጃቸው ላይ ደርሷል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉትም በብዙ መንገድ ጨለማ የከበበው የገጠሩ ማኅበረሰብ ሕይወት ዛሬ ብርሃን ማየት ጀምሯል። ይህ የብርሃን ፋና እየተቀጣጠለ ወደ ብዙኃኑ ሊደርስ የሁሉንም ፍላጎት አነሳስቷል። ሥሩ ከማለት ይልቅ ሠርቶ ማሳየትን የሚያስቀድመው የመደመር መንግስት የፈጠራቸው የገጠር ሞዴል መንደሮች ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን በዘላቂነት የሚያሳምሩ ናቸው። ሰላም እንሰንብት!
ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የአፍሪካ ኃያል ሀገር እየሆነች ነው-ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት
Aug 7, 2026 561
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት የመጪው ዘመን የአፍሪካ ኃያል ሀገር ወደመሆን እየተሸጋገረች ነው ሲል ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት ዘግቧል። ፈርስት ፖስት ሚዲያ ኢትዮጵያን በተመለከተ በሠራው ትንታኔው የሰው ዘር መገኛ፣የጥንታዊ መንግስታት ምድር፣የንግድ መስመሮች እና ከፍ ያለ የአፍሪካ ታሪካዊ መሰረት ያላት ሀገር መሆኗን አውስቷል። ሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ከቀድሞ ገናና ታሪኳ እኩል ታላቅ የሆነ አዲስ ምዕራፍ ለመገንባት በትጋት ላይ መሆኗን አንስቷል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት በቀጣናው እና የአፍሪካ ኃያል ሀገር መሆን የሚያስችላትን እንዲሁም የአህጉሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚበይንና የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሠራች መሆኗንም እንዲሁ። ለረጅም ዓመታት ዓለም ኢትዮጵያን የሚያውቃት በጦርነት፣በድርቅ እና በፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንደነበር በማስታወስ፥ዛሬ ግን ሀገሪቱ ይህንን የተዛባ ትርክት በኢነርጂ መሠረተ ልማት፣ በአቪየሽን፣ በማዕድን እና በዲጂታል ኢኮኖሚ አስደማሚ ለውጦች ለመቀየር እየሠራች ነው ብሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ተሻግራ እንዴት በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት ካላቸው ኢኮኖሚዎች ቀዳሚዋ ሆና ልትቀጥል ቻለች? የሚለውን ጥያቄ በማንሳትም በዝርዝር መልሶቹን ያብራራል። የዚህ ዋና ጥያቄ ዝርዝር ምላሽ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት እየተተገበሩ የሚገኙ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ ነው ያለው ሲል አንስቷል። • የመጀመሪያው የኢነርጂ አብዮት እና ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ነው። በዚህ የኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ጎልቶ የሚነሳው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሲሆን፣ ከ5 ሺህ ሜጋዋት በላይ የማመንጨት አቅም ያለው የአፍሪካ ትልቁ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት መሆኑን ፈርስት ፖስት በዘገባው ጠቅሷል። ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መሻቶች መሰረት፣የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የውጭ ምንዛሬ እና የቀጣናዊ ተጽዕኖ መፍጠሪያ አቅም መሆኑንም አብራርቷል። የሕዳሴ ግድብ ልዩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ከዓለም ባንክ ወይም ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አንድ ሳንቲም ሳይበደር በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም፣ ላብና ገንዘብ የተገነባ አፍሪካውያን በራሳቸው ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየነው ብሏል። ለኢትዮጵያውያን ግድቡ ከኮንክሪት እና ከተርባይን በላይ ትርጉም አለው ያለው ይህ የፈርስት ፖስት ዘገባ፥ እጅግ የላቀ እራስን የመቻል እና የኢኮኖሚ ነፃነት ማሳያ ሐውልት መሆኑንም ተንትኗል። ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን ለኬንያ፣ ለጂቡቲ እና ለሱዳን በመሸጥ ኤሌክትሪክን ወደ ከፍተኛ ገቢ ማመንጫነት እየቀየረች ከመሆኑም በላይ የመላው ምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የትስስር ማዕከል ሆናለች ነው ያለው። • የኢትዮጵያ የዕድገት ምሰሶ አቪዬሽን እና ቀጣናዊ ትስስር ኢነርጂ ብቻውን ኢኮኖሚያዊ አቅምን አይገነባም፤ ይልቁንም ኢነርጂ ኢንዱስትሪን ያነቃቃል፣ ትስስር ዓለም አቀፍ ንግድን ይመግባል ያለው ፈርስት ፖስት፥የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን ለላቀ የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ጉዞ መጀመሩን አንስቷል። በ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በየዓመቱ እስከ 110 ሚሊዮን ተጓዦችን እና ወደ 4 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ የዕቃ ጭነት ማስተናገድ አቅም አለው። ሙሉ በሙሉ ግንባታው ሲጠናቀቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከታላላቅ የአቪዬሽን ማዕከላት አንዱ ይሆናል ብሏል። ይህ ፕሮጀክት የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ መናኸሪያ የሆነችውን አዲስ አበባንና አፍሪካን፣ከሌሎች የዓለም ክፍሎች የሚያስተሳስር ዋና የመተላለፊያ ማዕከል እንደሚሆንም ተገልጿል። ስለዚህ አዲሱ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንት እና ለቱሪዝም፣ ለዓለም የዲፕሎሲ ትብብር ጉልህ ሚና እንዲያበረክት ታስቦ እየተገነባ ነው ብሏል። • የማዕድን ኢንቨስትመንትና በምግብ ራስን መቻል በሌላ በኩል ከኢትዮጵያ መሬት በታች ላለው የማዕድን ሀብቷ ትኩረት በመስጠት የልማት አብዮት እያካሄደች ስለመሆኑም ተንትኗል። ሀገሪቱ የወርቅና ሌሎች ማዕድናት ማውጫ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት አዳዲስ የውጭ ምንዛሬ ምንጮችን እያፈራች የማዕድን ኢንዱስትሪዋን እያሳደገች ነው። ወርቅ በፍጥነት ከኢትዮጵያ ቀዳሚ የወጪ ንግድ ምርቶች አንዱ በመሆን ለረጅም ጊዜ በግብርና ላይ ብቻ ጥገኛ ሆኖ የቆየውን ኢኮኖሚ ወደ ብዝኃ ዘርፍ እያሸጋገረ ይገኛል። በሌላ በኩል በምግብ ራስን ከመቻል ውጭ የትኛውም ኢኮኖሚያዊ ለውጥ የተሟላ ሊሆን አይችልም ያለው የፈረስት ፖስት ዘገባ፥ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆኑን ጠቅሷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን እንድትችል በጀመረው የለውጥ ጉዞ አስደማሚ ውጤት እያመጣ ነው ብሏል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከጉባ ብስራቶች አንዱ የሆነውና በሶማሌ ክልል እየተገነባ የሚገኘው የማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት በየዓመቱ 3 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ዩሪያ ማዳበሪያ ማምረት የሚችል ነው። ይህም ከውጭ የሚገባውን ማዳበሪያ ጥገኝነት በመቀነስ የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚያስችል አብራርቷል። "የምግብ ዋስትና የእኛ ስትራቴጂካዊ ጣልቃ ገብነት ነው።ያንን ግብ እውን ለማድረግ ግብአቶች ላይ መስራት አለብን።በግብአት ላይ መስራት ካልተቻለ የምግብ ዋስትናን እውን ለማድረግ መንገድ የለውም" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ በማካተት ዘገባው ሰፊ ሽፋን ሰጥቷል። ዲጂታላይዜሽን እና የኢንቨትመንትና የገበያ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ለውጥ ወደ ዲጂታልም እየተሸጋገረ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እንደተናገሩት የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠና ከዕቅዱ ቀድም ከመሳካቱም በላይ በርካታ ወጣቶች የዲጂታል እውቀት ባለቤት አድርጓል። በተመሳሳይ የዲጂታል ትስስር እየሰፋ ሲሆን የ4ጂ እና 5ጂ አገልግሎቶች በበርካታ ከተሞች ተደራሽ ሆኗል። ኢትዮጵያ ለበርካታ አስርት ዓመታት ተዘግተው የቆዩ እንደ ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ባንክ እና የካፒታል ገበያዎች ያሉ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጓንም አድንቋል። የካፒታል ገበያን መጀመሯም የግል ካፒታል ልውውጥን በማጎልበት ለኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተንትኗል። እነዚህ ማሻሻያዎች በአጠቃላይ በመንግስት ቁጥጥር ስር ከነበረው የኢኮኖሚ ወደ ግል ዘርፍ ኢንቨስትመንት እያደገ የሚሄድ ኢኮኖሚ መሰረታዊ ለውጥን እየተገነባ መሆኑን ያሳያሉ ነው ያለው። ኢትዮጵያ ካላት የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ አኳያ እድልና ፈተናዎች ከፊቷ መሆናቸውን በማንሳት፥ አዲሱን የዓለም አቀፍ የትብብር ጥምረት ብሪክስ አባል መሆኗን አውስቷል። ከቻይና፣ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት፣ ከምዕራባውያን አጋሮችና ከአፍሪካ ኢንቨስተሮች ኢንቨስትመንትን እየሳበች እንደምትገኝም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ጎራ ሳትለይ ከሁሉም የዓለም ሀገራት ጋር ትብብሯን እያጠናከረች ነው ብሏል። ዓለም ኢትዮጵያን የምታስታውሰው በጦርነት ቢሆንም፥ኢትዮጵያ ዓለም በአዲሱ የለውጥና የስኬት ጉዞዋ እንዲያስታውሳት እየሠራች ነው። ለዚህም በመላው ሀገሪቱ በሁሉም ዘርፍ ግዙፍ የኢኮኖሚ ሽግግር እየተካሄደ ሲሆን፥ ይህ የኢትዮጵያ ጉዞ ለቀጣዮቹ ዓመታት የቀጣናውንና የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊና አጠቃላይ ገጽታ በአዲስ መልኩ የሚቀርጽ ነው ሲል ፈርስት ፖስት ዘገባውን አብራርቷል።
ያቀደችውን በተግባር የምታሳካ ታላቅ ሀገር
Aug 3, 2026 869
የአንድ ሀገር ታላቅነት ከሚለካባቸው ጉዳዮች አንዱ የተያዙ ሀገራዊ እቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም ዋነኛው ነው። ኢትዮጵያም በዛሬው እለት በአንድ ጀምበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አዲስ ታሪካዊ ስኬት፣ ሀገሪቱ ያቀደችውን በተግባር ማሳየት የምትችልና ትልልቅ ህልሞችን የመተርጎም አቅም ያላት ታላቅ ሀገር መሆኗን ለመላው ዓለም በተግባር ያስመሰከረ ነው። ይህ በአንድ ጀምበር የተከናወነ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በርካታ ጥልቅ ትርጉሞችን የያዘ ነው፡ በአንድ ጀንበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ግዙፍ የሎጂስቲክስ፣ የዝግጅትና የህዝብ ንቅናቄ ስራን ይጠይቃል። ይህ ስኬት ሀገሪቱ ማንኛውንም ታላቅ አገራዊ እቅድ አቅዳ እስከ መጨረሻው የትግበራ ምዕራፍ ድረስ በብቃት የመምራትና የማስተባበር ተቋማዊና ህዝባዊ አቅም እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ዕድሜ፣ ጾታ፣ ወይም ልዩነት ሳይለያያቸው በአንድ ቀን ለተመሳሳይ አገራዊ ዓላማ መቆማቸው፣ ኢትዮጵያውያን ለጋራ እድገታቸውና ለሀገራቸው የወደፊት ተስፋ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትና አንድነት አሳይቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት ዋና ስጋት በሆነበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ እርምጃ ለችግሩ መፍትሔ በመስጠት ረገድ የዓለም አቀፍ መሪነቷን ያስመሰከረችበት አጋጣሚም ጭምር ነው። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የገጠሟትን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፈተናዎች ተሻግራ፣ አቅሟን አስተባብራ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ለዜጎቿም ሆነ ለውጭው ዓለም የሰጠችው ትልቅ የራስ መተማመንና የተስፋ መልእክት ነው። በአጠቃላይ፣ በአንድ ጀምበር የተከናወነው ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ አርቆ የማሰብና የማቀድ ችሎታዋን ብቻ ሳይሆን፣ ያቀደችውንም በአንድነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት በማውረድ በተግባር የምታሳይ ታላቅ ሀገር መሆኗን በግልጽ ያረጋገጠ አኩሪ ተግባር ነው።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ ትንሳኤ ብስራት!!
Aug 2, 2026 677
በሐዊ አጫሉ መግቢያ፡- የኢንዱስትሪ ዘርፍ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬን ከሚወስኑ ዋነኛ የብልፅግና ማረጋገጫ ምሰሶዎች መካከል በግምባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ዘርፉ ምርትን ከማሳደግ ባሻገር የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የሀገር ውስጥ ምርታማነትን የሚያፋጥን የልማት ሞተር ነው። ኢትዮጵያም ከግብርና መሠረት የተነሳ ኢኮኖሚዋን ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ሁሉን አቀፍ የምርት ሥርዓት ለማሸጋገር ከምታደርገው ጥረት መካከል ኢንዱስትሪውን በቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶነት በማካተት እየሰራችበት ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ አምስት ዐበይት የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት ምሰሶዎች ተመሥርቶ እየተመራ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥ ኢንዱስትሪው የምርት አቅምን በማሳደግ የግብርና ምርቶችን ወደ ተጨማሪ እሴት በመቀየርና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ እያስገኘ ነው። ይህንን ሽግግር እውን ለማድረግ የምርት አቅምን ማሳደግ፣ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር፣ የአቅርቦት ሰንሰለትን ማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና የሰው ኃይል ልማት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ የቀድሞ ገጽታ፤ ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ለውጥ መንገድ!! በቀደሙት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለያዩ ዕድሎችንና ፈተናዎችን በማስተናገድ በርካታ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል። ሀገሪቱን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር በተደረጉ ጥረቶች የተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተገንብተዋል። እነዚህ ፓርኮችም በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የተሞከረበት ወሳኝ ምዕራፍ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ ይህ ጉዞ በበቂ መሠረተ ልማት፣ በተሟላ የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና በተቀናጀ የምርት ሰንሰለት እጥረት ምክንያት በበርካታ ፈተናዎች ለመውደቅ ተገዶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ውስንነት፣ ዕውቅትና ክህሎትን የተሰላበሰ የሰው ኃይል አለመኖር፣ የፋይናንስ እጥረት፣ ውስብስብና አስቸጋሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትና የገበያ ትስስር እጥረት የዘርፉን እድገት ገድበው የነበሩ ሁነኛ ተግዳሮቶች ናቸው። ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ምርታማነት፤ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የለውጥ ፍኖት!! ባለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ ዘርፉ የተስተዋሉ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታትና የሀገሪቱን የማምረት አቅም ለማሳደግ አዳዲስ የለውጥ አቅጣጫዎች ተነድፈው ተተግበረዋል። በተለይም ኢንዱስትሪን ከተለመደው የምርት ሥርዓት በማሻገር ወደ ተወዳዳሪ ዘመናዊና ውጤታማ የማምረቻ ማዕከል ለመቀየር የተለያዩ የፖሊሲማሻሻያዎች ተደርገዋል። የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ፣ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን፣ የሰው ኃይል አቅምን ማሳደግና የግብርና-ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር በዘርፉ የተወሰዱ ሁነኛ የለውጥ እርምጃዎች ናቸው። በዚህም የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት በማጎልበት ከሀገር ውስጥ ገበያ እስከ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ድረስ ውጤት እያስገኘ ነው። የግል ባለሃብቱ ሚና፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሞተር!! የኢንዱስትሪ ልማት በመንግሥት ጥረት ብቻ የሚሳካ አይደለም። የግል ዘርፉ በካፒታል፣ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂና በአስተዳደር ብቃት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ለዘርፉ ዕድገት የማይተካ ሚና አለው። በዚህ ረገድ የግል ባለሃብቱ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዋና አጋር እንዲሆን የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተሻሽለው እየተሰራባቸው ይገኛል። ይህም የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት በማሻሻል፣ የንግድ ሥራ ሂደቶችን በማቀላጠፍ፣ የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋትና የምርት አቅምን በማሳደግ የግሉን ዘርፉ የምርታማነት አቅም እያጎለበተ ነው። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትንሳኤ ብስራት!! በሀገራችን የኢኮኖሚ አቅጣጫ ውስጥ የምርትና አገልግሎት አሰጣጥን በማቀናጀት አዲስ ምዕራፍ ከከፈቱ ዐበይት ሀገራዊ መርሃ-ግብሮች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተጠቃሽ ነው። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማምረት ባህልን በማሳደግ ዘርፉ ወደ አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚሸጋገርበት ሁነኛ ዕድልን ፈጥሯል። ንቅናቄው የማምረት አቅምን በማሳደግ ሥራ ያቆሙ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ መመለስ፣ የአምራቾችን ችግሮች በፍጥነት መፍታትና አዳዲስ ባለሃብቶችን ወደ ዘርፉ በመሳብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤ እያበረከተም ይገኛል። በዚህ ሂደት በፋይናንስ፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በውጭ ምንዛሬና በተቋማዊ ቅንጅት ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎች የአምራች ዘርፉን የምርታማነት አቅም በማጎልበት ጉልህ ሚና ተጫውቷል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲያንሰራራ በማድረግ የምርታማነት አብዮት እንዲቀጣጠል እያደረገ ይገኛል። የንቅናቄው ዋና ዓላማ በአምራች ዘርፉ የነበሩ ማነቆዎችን በመፍታት የኢትዮጵያን የማምረት አቅም ማሳደግ ነው። ይህም ሥራ ያቆሙ ወይም በአቅማቸው ልክ ያልሠሩ ፋብሪካዎችን ወደ ሙሉ ምርት በመመለስ የአምራቾችን ችግር በተቀናጀ መንገድ መፍታት፣ የፋይናንስና የግብዓት ተደራሽነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጓል። በዚህ ሂደት የማምረቻ ዘርፉ በአዲስ የሥራ ባህል፣ በተቋማዊ ቅንጅትና በፈጣን ውሳኔ አሰጣጥ እየተመራ መሆኑ የለውጡን ፍጥነት እያሳደገው ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ተደራሽነትን ማሻሻልና የምርት ጥራትን ማረጋገጥ የኢንዱስትሪው ትንሳኤ ዋና ማሳያዎች ናቸው። ለአብነትም፡- የፋይናንስ አቅምና የብድር አቅርቦት ማሻሻል፡- የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ እንቅፋት የሆነውን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ በተደረገው ርብርብ፣ የብድር አቅም ቀደም ሲል ከነበረበት 40 ቢሊዮን ብር ወደ 115 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ለአምራቾች ሰፊ የካፒታል አቅም መፍጠር ተችሏል። የውጭ ምንዛሬ ግኝትና የግብዓት ድጋፍ ማደግ፡- ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ይቀርብ የነበረው የውጭ ምንዛሬ መጠን አሁን ላይ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንዲደርስ ተደርጓል። ይህም ፋብሪካዎች ከአቅማቸው በታች እንዲሠሩ ያስገድድ የነበረውን የምርት ውስንነት በከፍተኛ ደረጃ አቃሎታል። የምርት ዕድገት፣ ተኪ ምርትና የኤክስፖርት አፈጻጸም፡- ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ ከነበረበት 348 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5.9 ቢሊዮን ዶላር በማደግ ግዙፍ ሀገራዊ ድል ተመዝግቧል። እንዲሁም በኤክስፖርት ገበያ የሚገኘው ገቢ ከ385 ሚሊዮን ዶላር ወደ 607 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ማለት ችሏል። ተቋማዊ ቅንጅትና አዲስ የሥራ ባህል ማዳበር፡- በክልሎችና በፌዴራል ተቋማት መካከል የነበረውን የቢሮክራሲ ጫና በመቀነስ ፈጣን ውሳኔዎች እንዲሰጡ መደረጉ፤ እንዲሁም ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርትን በኩራት የመጠቀም እና የሀገር ፍቅር ስሜትን ከአምራችነት ጋር የማስተሳሰር ትልቅ ማህበራዊ ንቃተ-ህሊና መገንባት ተችሏል። የወደፊት ተስፋ፤ ኢትዮጵያ አዲሲቷ አፍሪካዊት የኢንዱስትሪ ምርታማነት ተምሳሌት ሀገር!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ በቀጣይ ዓመታት ከተለመደው ማምረት ወደ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ሥርዓት እንዲሸጋገር ይጠበቃል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሜሽን፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና የፈጠራ ሥርዓቶችን ወደ ማምረቻ ዘርፉ ማስገባት የወደፊቱ ትኩረት ይሆናል። በተመሳሳይም ጠንካራ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስር፣ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት፣ ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአህጉራዊ ገበያ ተደራሽነት የሀገሪቱ ቀጣይ የኢንዱስትሪ ግቦች ናቸው። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) የሚፈጥረውን ሰፊ የገበያ ዕድል በመጠቀም ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችል መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ማጠቃለያ፡- ማምረት፤ የኢትዮጵያ የብልፅግና ቁልፍ መሳሪያ!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ተጨማሪ እሴት ያለው ምርት አቅራቢነት በማምራት እመርታዊ ውጤቶችን እያስገኘ ነው። የኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ማለት ፋብሪካዎችን ብቻ ማስፋፋት ሳይሆን የሀገርን ምርታማነት፣ የወጣቶችን ዕድል፣ የኢኮኖሚ ነፃነትንና የልማት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን የዛሬ ልማት ብቻ ሳይሆን የነገውን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚገነባ ሀገራዊ ራዕይ ነው።
ትንታኔዎች
ከአረንጓዴ አሻራ እስከ ዓለም ገበያ - የኢትዮጵያ ቡና ልማት አዲስ የዕድገት ምዕራፍ
Aug 13, 2026 262
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቡና መገኛ ከመሆኗም ባለፈ ምርቱ አሁንም ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብትና ማህበራዊ ህይወት ትልቅ መሰረት ያለው ነው። የዓለም የቡና ዝርያዎች ሁሉ መገኛ የሆነው የአረቢካ ቡና ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘውም በኢትዮጵያ እንደሆነ ይታወቃል። በኢትዮጵያ ቡና መጠጣት የዕለት ተዕለት ባህል ሲሆን፣ የቡና አፈላል ስነ ስርዓት ሰላምን፣ አንድነትንና ማህበራዊ ውይይትን የሚያጠናክር ትልቅ እሴት ተደርጎም ይወሰዳል። በአሁኑ ወቅት ቡና ለሀገሪቱ ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኝ ቀዳሚው የግብርና ምርት በመሆን ማዕከላዊ የኢኮኖሚ ሚናውን እየተጫወተ ይገኛል። አብዛኛው የኢትዮጵያ ቡና የሚመረተው በተፈጥሯዊ መንገድ በገበሬዎች ማሳ ላይ ወይም በዱር ውስጥ በመሆኑ፣ ለሰው ሰራሽ ማዳበሪያና ኬሚካል ተጋላጭ አይደለም። ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተመራጭነት ይበልጥ ከፍ አድርጎታል። ከኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ምሰሶ አንዱ የሆነው ቡናችን ለሀገሪቷ እያስገኘ ያለው ገቢም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ካነሷቸው ጉዳዮች መካከልም አንዱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዋልታ የሆነው ቡና ነበር። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከብራዚልና ኮሎምቢያ በመቀጠል በዓለም 3ኛዋ ትልቋ የቡና ላኪ ሀገር መሆኗን እና በአፍሪካም ቀዳሚ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጸዋል። በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ከቡና ወጪ ንግድ 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን፣ ይህ ውጤት ባለፉት 17 ዓመታት በድምሩ ከተገኘው 3 ነጥብ3 ቢሊዮን ዶላር ጋር ሲነጻጸር በዘርፉ የተመዘገበውን ከፍተኛ ዕድገት ያሳያል ብለዋል። ለተመዘገበው ውጤት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም አጠናክራ መጠቀም እንዳለባት ተናግረዋል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ የኢትዮጵያን የቡና ዘርፍ ከዘልማዳዊ አሰራር ወደ ዘመናዊ ምርታማነት ለማሸጋገር የሚያስችል አዲስ የ10 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ እና የተሻሻለ የልማት ፓኬጅ መዘጋጀቱን በቅርቡ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል። ቡና በሀገሪቱ ኢኮኖሚ፣ የሚሊዮን አርሶ አደሮች የኑሮ መሠረትና የወጪ ንግድ ዋነኛ ምሰሶ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ታላቅ ሀብት በጥራትና በዘላቂነት በማሳደግ ከምርት ወደ እሴት፣ ከእሴት ወደ ዓለም ገበያ ማሸጋገር የዘርፉ ዋነኛ አቅጣጫ መሆኑን ተናግረዋል። ይህንኑ ስትራቴጂ ለማሳካት የተጀመረው ሃገራዊ የቡና ምርትና ምርታማነት ኢኒሼቲቭ በአሁኑ ወቅት በሔክታር 9 ኩንታል የሆነውን የቡና ምርታማነት ወደ 21 ኩንታል ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ሚኒስትሩ አብራርተዋል። በተጨማሪም በ 1 ነጥብ15 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ላይ የቡና ልማት ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን፣ ለዚህም ምርጥ የቡና ዘር አጠቃቀም፣ የተቀናጀ የአፈር ንጥረ-ነገር፣ የቡና ተክል ጥግግት፣ የገረዛና የጥላ ዛፍ አያያዝ፣ የተቀናጀ የተባይ መከላከል፣ የመስኖ፣ የማዳበሪያ እንዲሁም የተሻሻለ የምርት አሰባሰብና የዕድሳት ሥራዎችን ያካተቱ ዘጠኝ የትኩረት መስኮች ተለይተው ወደ ሥራ መግባታቸውን አመልክተዋል። ይህ አዲሱ የቡና ልማት ኢኒሼቲቭ አርሶ አደሮችን፣ የማህበራትንና የባለሙያዎችን ግንዛቤና አቅም ለማሳደግ ሰፊ የንቅናቄ ሥራዎችን እንደሚከናውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በቡና ወጪ ንግድ ከአፍሪካ ቀዳሚና ከዓለም 3ኛዋ ትልቅ ላኪ ሀገር በመሆን ያሳየችው እመርታ፣ የዘርፉን ታላቅ የምጣኔ-ሀብት አቅም በተጨባጭ የሚያሳይ ነው። ለዚህ ደግሞ ላለፉት ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ምህዳር በማስተካከል ረገድ የራሱን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ይታወቃል። በዚህም መርሃ-ግብሩ በተጀመረበት 2011 ዓ.ም 600 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የተተከለው የቡና ችግኝ በየዓመቱ እያደገ በመሔድ በ2017 ዓ.ም ላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሸፈን ተችሏል። ይሄ በመሆኑም የቡና ምርታማነት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል። በ2011 ዓ.ም. ግማሽ ሚሊዮን ቶን የነበረው ዓመታዊ የቡና ምርት 2017 ዓም ላይ ወደ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ምርት ማግኘት በመቻሉ ኢኮኖሚው ላይ ያለውን ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ማስቀጠል ችሏል። በመሆኑም፣ የተያዘውን የተቀናጀ የልማት ስትራቴጂ በተግባር በመተርጎም የቡናን ምርት በጥራትና በብዛት ማሳደግ፣ የሀገሪቱን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት ከመደገፍ ባለፈ የኢትዮጵያን ቡና የወደፊት ጉዞ እና ዓለም አቀፋዊ መሪነት እጅግ አስተማማኝ ያደርገዋል።
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዞ አንዱ መገለጫ -መሶብ
Aug 12, 2026 310
(በሙሴ መለሰ) የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች መመላለስ፣ የወረቀት ክምርና ረጅም ሰልፍ የኢትዮጵያውያን የቆየ የዕለት ተዕለት ፈተና ነበር። ይህንን የዜጎች እንግልት በዘላቂነት ለመቅረፍ እና አሰራርን ለማዘመን ታስቦ የተመሠረተው መሶብ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል። የተቀናጀው የ"አዲስ መሶብ" ሱፐር አፕ (Super App) ዲጂታል መድረክ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ወደ ሙሉ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። የመሶብ ዋና ዓላማ ተበታትነው የነበሩ ልዩ ልዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ አጋዥነት በአንድ ጣሪያ ስር ማገናኘት ነው። ዜጎች ጊዜና ገንዘባቸውን ሳይባክኑ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ፣ የሰዎችን ቀጥተኛ ንክኪ በመቀነስ ሙስናና ብልሹ አሰራርን መዋጋት፣ እንዲሁም ግልጽነትን ማስፈን የተቋሙ መሠረታዊ ምሰሶዎች ናቸው። በረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ደግሞ እያንዳንዱ ዜጋ በብሔራዊ የፋይዳ (Fayda) መታወቂያው ብቻ በመጠቀም ሁሉንም የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ አካውንት እንዲያገኝ ማድረግ እና ሥርዓቱን ለአፍሪካ ሀገራት እንደ መሪ ተሞክሮ ማቅረብን ያለመ ነው። ይህ የዲጂታል መድረክ እና አጠቃላይ የቴክኖሎጂ ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሀገር በቀል እውቀት የበለጸገ ሲሆን፣ ጥቅም ላይ የዋሉት የሶፍትዌር ቴክኖሎጂዎች ለሁሉም ክፍት የሆነ (Open-source) መሆናቸው ተቋሙን ከከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ አድኖታል። በማዕከላቱ ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች ጥብቅ የሆነ የምልመላ ፈተና እና ልዩ ስልጠናዎችን አልፈው የሚገቡ በመሆናቸው የአገልግሎት ጥራቱ ከብልሹ አሰራር የፀዳ እንዲሆን አስችሏል። መጀመሪያ ላይ በ12 ተቋማትና በ41 አገልግሎቶች ብቻ የተጀመረው ይህ ዘመናዊ አሰራር፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እያሳየ ባለው ፈጣን እድገት በአሁኑ ወቅት የትስስር አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችሏል። አሁን ባለው ተጨባጭ ቁመና መሶብ 27 ዋና ዋና የመንግሥት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መስመር ማገናኘት የቻለ ሲሆን፣ እነዚህ ተቋማት በአንድ ላይ በመቀናጀት ከ288 በላይ የተለያዩ ዲጂታል አገልግሎቶችን በጥራትና በፍጥነት እያቀረቡ ይገኛሉ። ተገልጋዮች እንደ ፓስፖርት፣ ውክልና፣ የንግድ ፈቃድ እና የሰነዶች ማረጋገጫ ያሉ ወሳኝ ጉዳዮቻቸውን በአንድ ማዕከል ወይም በሞባይል መተግበሪያቸው ማከናወን ይችላሉ። ይህንን ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ100 በላይ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ማዕከላት የተቋቋሙ ሲሆን፣ እስካሁንም ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በማስተናገድ የአገልግሎት እርካታውን በፌዴራል ደረጃ ወደ ከ98 በመቶ በላይ ማድረስ ተችሏል። በቅርብ ቀናት ውስጥ የወጡ አዳዲስ ወቅታዊ መረጃዎች ደግሞ ተቋሙ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ እና ተለዋዋጭ እያደረገው መሆኑን ያሳያሉ። በቀን የሥራ ሰዓት መስተናገድ ለማይችሉ ሠራተኞችና ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ከተለመደው የሥራ ሰዓት ውጭ የምሽት አገልግሎት (Night Service) በይፋ ተጀምሯል። ከዚህ በተጨማሪ ወደ ማህበረሰቡ በቀጥታ በመሄድ አገልግሎት የሚሰጡት እና የራሳቸውን ኃይል በከፊል ከፀሐይ ብርሃን የሚያመነጩት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ አውቶቡሶች (Mobile Mesob Bus) በተለይ ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች የቤት ለቤት አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። የጤናው ዘርፍ አገልግሎቶችንም ለማካተት ከቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ጋር አዲስ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ ወደ ሀገር ለሚገቡ ባለሃብቶችና ዳያስፖራዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በቦሌ ዓለም አቀፍ አየውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ማዕከል እየተገነባ ይገኛል። በአዲስ አበባ ከተማም ከ480 በላይ የአገልግሎት መስኮቶች የሚኖሩት አንድ ግዙፍ ማዕከላዊ የኮምፕሌክስ ሕንፃ ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ ነው። “ዩኒፋይድ መሶብ” የተሰኘው የኦንላይን መድረክ ዜጎች በሞባይል ስልካቸው የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችል ሥርዓትም ተግባራዊ ሆኗል። በአሁኑ ወቅት መሶብ ከሀገር ውስጥ አልፎ ዓለም አቀፍ ትኩረትን እየሳበ ይገኛል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቤኒን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን ማዕከሉን በይፋ የጎበኙ ሲሆን፣ መሶብ ለአፍሪካ ሀገራት በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመንግሥት አገልግሎት ሥርዓት ለመገንባት እንደ ትልቅ የምርጥ ተሞክሮ ማሳያ እየተወሰደ ነው። በቀጣይም ከጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ጋር በዲጂታል አገልግሎት ዙሪያ የጋራ ትስስር በመፍጠር የአህጉር አቀፍ የዲጂታል ሥርዓት የመገንባት ስትራቴጂ ተነድፎ እየተሰራ ይገኛል። በአጠቃላይ መሶብ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን እና የሕዝብን እንግልት በመቀነስ ረገድ ውጤታማነቱን በተግባር ያረጋገጠ ስኬታማ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማሳያ ነው።
ወዳጅነት ፓርክ ፦ የመደመር እሴት ማሳያ
Aug 11, 2026 231
በሙሴ መለሰ በአዲስ አበባ መሐል የሚገኘው የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት ስምንት ዓመታት ከተገነቡት የመጀመሪያዎቹ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች አንዱ ነው። ይህ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውና 56 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ባለው የ“ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት” (Beautifying Sheger Project) ስር የተከናወነ ነው። ፕሮጀክቱ በሁለት ዋና ዋና ምዕራፎች ተከፍሎ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ሊጠናቀቅ ችሏል። ኢትዮጵያ የጀመረችው ይህ የከተማ ውበትና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ የውበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ሀብት ፈጣሪ መሆኑንም በተግባር ያረጋገጠ ህያው ማሳያ ነው። የወዳጅነት አደባባይ የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሂደት በ2011 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የቆሻሻ ማጠራቀሚያና ክፍት ቦታ የነበረውን ስፍራ ወደ ዘመናዊ አረንጓዴ ሥነ-ምህዳር ለመቀየር ያለመ ነበር። ግንባታው በ11 ወራት ብቻ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ በጳጉሜ 2012 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በቀድሞዋ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል። ይህ ክፍል 32 ሄክታር መሬት በማልማት፣ አሳ እና ዳክዬዎች የሚቀዝፉበት ሰው ሠራሽ ሐይቅ፣ ትልቅ አደባባይ (Square)፣ እና 1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻን መልሶ ማቋቋምን ያካተተ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ለምሽት መዝናኛ የሚሆን ማራኪ የፏፏቴ ላይ የብርሃን ትርኢት (Dancing Fountain)፣ ከ16 በላይ የውጪ ላይ ስብሰባ ማካሄጃ ቦታዎች (Event Venues)፣ የሰርግ አፀዶች፣ ካፌዎች፣ የፎቶ ስቱዲዮዎች እና ጠዋት ጠዋት የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ሩጫ ለማድረግ ምቹ የሆኑ የተከለሉ መንገዶችን ይዟል። ምዕራፍ አንድ ከተመረቀ በኋላ ወዲያውኑ የሁለተኛው ምዕራፍ (Friendship Park 2) የዲዛይንና የዝግጅት ሥራዎች ተጀምረዋል። በግንባታው ወቅት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም፣ ከሌላ ቦታ የተሰባሰቡ ከ4ሺህ በላይ አገር በቀል ትልልቅ ዛፎች (Indigenous trees) መጥተው በቦታው ላይ በተሳካ ሁኔታ እንዲተከሉ ተደርጓል። ግንባታው በጥቅምት 2015 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተመርቋል። 16 ሄክታር መሬት የሸፈነው ይህ ክፍል ከአብርሆት ቤተ-መጽሐፍት ፊት ለፊት የሚገኝ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ለሕፃናት፣ ለታዳጊዎችና ለቤተሰብ ስፖርታዊ መስተጋብር ተለይቶ የተገነባ ነው። በውስጡም እጅግ ዘመናዊና ሰፊ የሕፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን (Playgrounds)፣ ታዳጊዎች እየተጫወቱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን የሚለማመዱበትን የሳይንስ ማዕከል፣ ትንንሽ የእግር ኳስ (Mini-football) እና የቅርጫት ኳስ (Basketball) ሜዳዎችን፣ የሩጫ ትራኮችን፣ ለወጣቶች ንባብ የሚሆኑ ቦታዎችን (Reading nooks) እና ከጎኑ ያለውን የሳይንስ ሙዚየም ግንባታን ያካተተ ሰፊ ይዘት አለው። የወዳጅነት ፓርክ ከብሔራዊ ቤተመንግሥት እስከ መስቀል አደባባይባለው አካባቢ የሚዘልቅ ዘመናዊ የሕዝብ መገልገያና መዝናኛ ማዕከል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ ይህ ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ ማስገኘት ችሏል። ይህም የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ራሳቸውን ችለው ከፍተኛ ገቢ ማመንጨት ከመቻል ባለፈ፣ በቱሪዝም ዘርፉ፣ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዘንድ ለበርካታ ዜጎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሰፊ የሥራ ዕድል እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እየፈጠረ ይገኛል። ከዚህ ኢኮኖሚያዊ እሴቱ ባሻገር፣ ፕሮጀክቱ የከተማ ነዋሪዎችን ማኅበራዊ ትስስር በከፍተኛ ደረጃ ያጠናክራል፤ የዜጎችን የኑሮ ጥራት፣ የጤና ሁናቴ እና ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ (Life style) ከማሻሻል አንጻርም የመደመር እሴት በተግባር መሬት ማወረዱንና የዜጎችን አገራዊ የባለቤትነት ስሜት በጽኑ የሚያሳድግ ትልቅ ማሳያ ነው። ፓርኩ ለጤና፣ ለአካል ብቃት፣ ለመዝናኛና ለንባብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ወጣቶች ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን በስፖርት፣ በዕውቀት ቀሰማና በሌሎች በጎ ነገሮች ላይ እንዲያሳልፉ ምቹ ከባቢ ፈጥሯል። በተጨማሪም ቦታው ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎችና ጎብኝዎች በየቀኑ በስፋት የሚገናኙበት ማዕከል መሆን ችሏል። በስፍራው ከቤተሰቦችና ሕፃናት፣ ከስፖርት ቡድኖችና ከሠርግ ተካፋዮች ጀምሮ እስከ ዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎች በከፍተኛ ቁጥር ይገኙበታል። ይህም ለሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች (Content Creators) ምቹ ከባቢ በመፍጠር፣ የአዲስ አበባን ዘመናዊና ማራኪ ገጽታ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት እንዲያስተዋውቁና የከተማዋን በጎ ስም ለዓለም እንዲያደርሱ ትልቅ ዕድል ከፍቷል። ይህ ፓርክ አዲስ አበባን ለሌሎች የክልል ከተሞች በአረንጓዴ ልማት፣ በጽዳትና በዘመናዊ የሕዝብ መገልገያዎች በሞዴልነት የሚጠቀስ ሲሆን፣ የከተማዋን የዲፕሎማሲያዊ መዲናነት ገጽታ ይበልጥ በማደስ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች፣ ለዲፕሎማቶችና ለዓለም አቀፍ እንግዶች በጣም ሳቢና ተመራጭ መዳረሻ አድርጓታል። ፓርኩ በከተማዋ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ውስጥ እየተገነቡ ላሉ ተመሳሳይ የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ቀዳሚ ማሳያ ሲሆን፣ እነዚህ አዳዲስ ቦታዎች እሴት የሚፈጥሩ፣ ዕድሎችን የሚያመቻቹ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያንን ባለቤትነት የሚያረጋግጡ ማዕከላት መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ያረጋግጣል።
የኮደሮች ኢኒሼቲቭ፡ የኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታና የወጣቶች ብሩህ መፃኢ ዕድል
Aug 10, 2026 250
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በዲጂታሉ ዓለም ያላትን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እና የወጣቶችን ክህሎት ለማልማት ያለመው የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ተጀምሯል። ይህ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች መካከል በተደረገ ትብብር የተዘጋጀ ሀገራዊ የዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ ፕሮጀክት ነው። ዋና ዓላማውም ወጣቶች በዲጂታሉ ዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆኑና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈለጉ የቴክኖሎጂ ክህሎቶችን እንዲጨብጡ ማስቻል ነው። የስልጠናው መርሃ ግብር በኦንላይን ”Udacity” በተሰኘ ዓለም የትምህርት መድረክ በኩል የሚሰጥ ሲሆን፣ በዌብ ዲቨሎፕመንት፣ በዳታ አናሊቲክስ እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዋና ዋና ዘርፎች የተከፈለ ነው። ከእነዚህም ጎን ለጎን የንግድና ሥራ ፈጠራ እንዲሁም የመሪነት ክህሎት አጫጭር ስልጠናዎች ተካተዋል። እያንዳንዱ ኮርስ በግል ፍጥነት የሚወሰድ ሆኖ በአማካይ ከ6 እስከ 7 ሳምንታት የሚወስድ ሲሆን፣ ስልጠናውን በጥሩ ሁኔታ ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ሙሉ በሙሉ በነፃ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው የ’Udacity’ እና የኢኒሼቲቩ ይፋዊ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ይሰጣል። በዚህ ፕሮግራም ላይ ዕድሜው ከ13 ዓመት በላይ የሆነ ማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ የቀደመ የኮዲንግ እውቀት ሳይጠይቀው መመዝገብ ይችላል። ለመማር የሚያስፈልጉት ነገሮች የኢንተርኔት ግንኙነት ያለው ኮምፒውተር ወይም ስማርትፎን ብቻ ሲሆኑ፣ ምዝገባውም በይፋዊው 5millioncoders.gov.et ድህረ ገጽ በኩል ይከናወናል። የኢኒሼቲቩ የመጨረሻ ግቦች ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ እና በመላው አህጉር ውስጥ የቴክኖሎጂ ማዕከል ማድረግ እና የዲጂታል ስትራቴጂዎችን ማሳካት ናቸው። በተጨማሪም ሰልጣኞች በሀገር ውስጥና በውጭ ድርጅቶች እንዲቀጠሩ፣ ከቤት ሳይወጡ በዶላር የሚከፍሉ የርቀት ስራዎችን እንዲሰሩ እና የራሳቸውን የቴክኖሎጂ ስታርታፕ እንዲመሰርቱ መንገድ ይከፍታል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ የሚታየውን የክህሎት እጥረት በመሙላትና ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ገቢ በማስገኘት የወጣቶችን ተወዳዳሪነትና በራስ የመተማመን አቅም ያሳድጋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት ሀገራዊ ጥሪ፣ ይህ ክረምት በከንቱ እንዲያልፍ ሳይፈቀድ ወጣቶች በነጻ የሚሰጠውንና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለውን ትምህርት እንዲወስዱ አሳስበዋል። አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ቀድመው የወሰኑ በመሆናቸው፣ ሌሎችም ይህንን እድል በመጠቀም የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት የተሳታፊዎችን ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ለማድረስ የቀረበውን ጥሪ እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል። ይህንን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል። ዝግጅቱ የዘርፉን መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጭዎችን፣ የምስክር ወረቀት ያላቸውን የኢኒሼቲቩን ተመራቂዎች እና ወጣት ባለሙያዎችን በአንድነት ያገናኘ ሲሆን፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ ባተኮረ የኤግዚቢሽን ጉብኝት ተጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ሥዩም የመክፈቻ ንግግር ቀጥሏል። ኃላፊዋ የወጣቶች የቴክኒክና የዲጂታል ክህሎት ብቃት ወሳኝ ሀገራዊ ሀብት መሆኑን ገልጸው፣ የኮደሮችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የቀረበውን ጥሪ ተግባራዊነት አረጋግጠዋል። ቀጥሎ በተካሄደው የፓናል ውይይት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር አብዮት ባዩ፣ የጊሮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቤተልሔም ደሴ፣ እንዲሁም የኢኒሼቲቩ ምሩቃን የሆኑት አዝመራው ታደሰ እና የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ማኅሌት ሥዩም ልምዳቸውንና እይታቸውን አካፍለዋል። ፓናሊስቶቹ ወጣቶች ክህሎታቸውን ያለማቋረጥ እንዲያሳድጉ እና በኢትዮጵያ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር ዕድገት ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ያበረታቱ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩም የኢኒሼቲቩን ከፍተኛ ሀገራዊ ሚና በድጋሚ ያረጋገጠ ሆኖ ማለፉን ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያላትን ራዕይ ለማሳካት የተጣለ ትልቅ መሰረት ነው። ወጣቶች በቴክኖሎጂው ዘርፍ የሚጨብጡት ዕውቀት የራሳቸውን የፈጠራ መንገድ ከመክፈቱም በላይ፣ ሀገሪቱ በምስራቅ አፍሪካና በአህጉሪቱ የቴክኖሎጂ ማዕከል ሆና እንድትወጣ ያስችላታል። በመሆኑም ይህን አጋጣሚ በአግባቡ መጠቀም ለሀገሪቱ ዘላቂ እድገትና ለወጣቱ ብሩህ ተስፋ ወሳኝ እርምጃ ነው።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 11784
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 21592
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14619
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20371
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
በምክክር እንጂ በመሳሪያ ድምጽ ሀገር አይገነባም
Aug 8, 2026 490
ኢትዮጵያ የዛሬ ማንነቷና ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እዚህ እንድትደርስ በርካታ ውጣውረዶችን አልፋለች። በቀደመ ታሪኳም ዜጎች በራሳቸው የውስጥ ጉዳይ መስማማት ባለመቻል እርስ በእርስ ካደረጓቸው ግጭቶች ባለፈ የውጭ ሃይሎችም የራሳቸውን አሉታዊ ጫና ሲፈጥሩ ቆይተዋል፤ አሁንም ይህንኑ ለማስቀጠል ተላላኪዎቻቸውን ለመጠቀም ሲሞክሩ ይታያል። በአንድ ሃገር ውስጥ የማያግባቡ ጉዳዮች በየትኛውም አጋጣሚና የታሪክ ምዕራፍ ሊያጋጥሙ ይችላሉ። እነዚህን ችግሮች በሃይል ለመፍታት የሚደረገው የመሳሪያ ትንቅንቅ ግን አክሳሪና ዘመን እያለፈበትም ነው። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ሰላማዊ የእድገት ጉዞ ለማወክ የህዝቦቿን አንድነት ለመበጥበጥ ከቅርብም ሆነ ከሩቅ የሚመጡ ጠላቶች ጠፍተው አያውቁም። በየዘመናቱ የተሻገርናቸው የታሪክ ስብራቶችን ፣ የመብት ጥያቄዎችንና ሌሎችንም መነሻ በማድረግ በውስጥ ባንዳዎች እና በውጭ ባዳዎች አማካኝነት የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ለመክተት፣ የብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚደረጉ ሴራዎች ዛሬም ላይ ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት ተሰሚነትና ተጽዕኖ የሚያሳምማቸው ለዜጎቿን እኩል ተጠቃሚነትና ብልጽግና መረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚያስጨንቃቸው እነዚህ ሃይሎች በመብት ፣ በነጻነት፣ በዴሞክራሲ፣ በማንነትና በሌሎችም የሃሰት ትርክቶች መነሻነት በሩቅ ቢያቅታቸው በቅርብ የውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን እያደራጁ በጀት መድበው የጦር መሳሪያ አቅርበው ሀገር የማፍረስ ሙከራቸውን አላቋረጡም። በመደመር እሳቤ ሁሉንም በአንድ ላይ በማቀራረብና የጋራ ትርክቶችን በመገንባት ከልዩነት ይልቅ የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ዘላቂ ልማቷን መፃኢ ብሩህ ተስፋዋን ለማለምለም በሁሉም ዘርፍ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ተሳትፎ እየሰራች መሆኗም ምቾት ነስቷቸዋል። በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሔደ ያለውና ወርቃማው እድል ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ፣ የሚያስችሉ ወሳኝ ምዕራፎች ላይ ደርሷል ። በዚህ የምክክር ሒደት በሀገሪቱ የትኛውም ጥግ ያለ ዜጋ እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የተወከሉበት ፣ የብሔር፣ የፖለቲካ አመለካከትና የሃይማኖት ልዩነት የማያደናቅፉት ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እየተካሔደ ይገኛል። ጥያቄያችንን በጠብመንጃ አፈሙዝ እንፈታለን ያሉ ታጣቂዎችም ብረት በማስቀመጥ አጀንዳዎቻቸውን ይዘው ወደ ጠረጴዛው ቀርበዋል። ልክ ናቸው ሀገር ከሁሉም ነገር ትበልጣለችና ይሄንን ወርቃማ እድል ለመጠቀም ማሰብ ትክክለኛው ውሳኔ ነው። በትጥቅ ትግል ጥያቄያችንን እንመልሳለን በሚል ሽፋን የሌሎችን አጀንዳ ለማሳካት የሚደረግ ጥረት የሃገርና የትውልድ ጠባሳ ከማስቀመጥና የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው መገንዘብ ብልህነት ነው። የዚህ ምክክር ተሳታፊ/ተመካካሪ ከሆኑት የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) አመራር ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በዚህ ይስማማሉ ። ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ተስፋ የጣልንበት፣ በንግግር፣ በምክክር ሀገራችንን የምናስቀጥልበት፣ ሁሉም ተነጋግሮ ተመካክሮ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ከችግሮች ነፃ የሚያደርግበት ነው ይላሉ። ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚነጋገርበት፣ የሚመካከርበት እና በሃሳብ የበላይነት ጠንካራ ሃገር የሚፈጠርበት መልካም የታሪክ አጋጣሚ መሆኑንም ይናገራሉ። በምክክር፣ በድርድር የሕዝብን ጥያቄ በመመለስ ሀገርን የምናስቀጥልበትና የውጭ ኃይሎችን ጣልቃ ገብነት የምናስወግድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ነው ብለዋል። የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራር የቀድሞ ታጣቂ ጃል ሰኚም ይሄንኑ ሃሳብ ይጋራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ለዓመታት የቆዩ ልዩነቶችን ለመፍታት ሀገራዊ ምክክር መዘጋጀቱ ትልቅ እርምጃ እንደመሆኑ እሳቸውም ያላቸውን ሀሳብ በማንጸባረቅ እየመከሩ ይገኛሉ። እርሳቸውና ቡድናቸው ከዚህ ቀደም የትጥቅ ትግልን በመምረጥ ጫካ ገብተው እንደነበር አስታውሰው፤ ችግሮችን በመሳሪያ ከመፍታት ይልቅ በሰላማዊ የምክክር መድረክ መፍታት ጥሩ አማራጭ መሆኑን አምነው ወደ ሰላም መንገድ መምጣታቸውንም ተናግረዋል። ችግሮቻቸውን በምክክር የፈቱ ሀገራት በሁሉም ዘርፍ ዕድገታቸውን የሚያስቀጥሉ ሲሆኑ ወደ ትጥቅ ትግል ያመሩና ግጭት ውስጥ የገቡት ደግሞ በፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውድቀት ለከፋ ድህነት መዳረጋቸውን ጠቅሰዋል። የጦር መሣሪያ በመነቅነቅና ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ በመግባት የሚፈታ ችግር እንደሌለ የሚናገሩት ደግሞ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ(አብን) አመራሩ ተመካካሪ ጣሒር መሀመድ ናቸው። ጫካ ባለውና እዚህ ባለው ሰው መካከል ምንም ዐይነት የዜግነት ልዩነት እንደሌለ ገልጸው ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሃሳብ ለመታገል ልዩነቱን ለማቅረብ የፈለገ ሁሉም ዜጋ በምክክሩ የመሳተፍ ነጻነት እንዳለው ገልጸዋል። በሃገራዊ ምክክሩ ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሰላማዊ መድረክ መወያየት የተመረጠበት ዋና ምክንያት ዘላቂ ሰላም፣ አገራዊ መግባባት እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ ለማምጣት ነው:: የትጥቅ ትግል የዜጎችን ህይወት ያጠፋል፣ መሰረተ ልማቶችን ያወድማል፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድቀትንም ያመጣል: ፤ ሰላማዊ መድረክ ግን ያለምንም ደም መፋሰስ ሃሳብን በሃሳብ ለመሞገት እድል ይሰጣል:: በኃይል የሚመጣ ለውጥ ብዙውን ጊዜ አሸናፊና ተሸናፊን ስለሚፈጥር የቁስል እና የቂም ዑደትን ያስቀጥላል:: በሰላማዊ ውይይት የሚገኝ መፍትሄ ግን የሁሉንም ወገን ስጋት እና ፍላጎት ያገናዘበ በመሆኑ ዘላቂነት ይኖረዋል:: ሃገራዊ ምክክሩ የታጠቁ አካላትም ጭምር መሳሪያቸውን አስቀምጠው በሃሳብ እንዲፎካከሩ መንገድ ከፍቷል። ይህ ታሪካዊና ወርቃማ እድል ኢትዮጵያዊንን አግባብቶ ወደተረጋጋችና የበለጸገች ሃገር የሚመራ በመሆኑ ስኬታማነቱ አያጠራጥርም። ለእድለኛው ትውልድ ያጋጠመው ወርቃማው ስጦታ ሃገራዊ ምክክር የተቋቋመለትን ዓላማ ያሳካል።
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 1358
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።