ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የልብ በሽታን መከላከል የሚያስችል የሕክምና አቅምን የመገንባት ሥራ ላይ ትኩረት ተደርጓል
Aug 1, 2026 12
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት የልብ በሽታን መከላከል የሚያስችል የሕክምና አቅምን ለመገንባት እየሠራ እንደሚገኝ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ባለሙያዎች ማኅበር (ESCP) እና የፓን-አፍሪካ የልብ ሕክምና ማኅበር (PASCAR) በጋራ ያዘጋጁት "የESCP–PASCAR ኮንግረስ 2026" ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል፡፡ ጉባኤው በአፍሪካ የልብና የደም ሥር ጤናን ለማጠናከር፣ ሳይንሳዊ እውቀትን ለመለዋወጥና የባለሙያዎችን ትብብር ለማጎልበት ያለመ ነው። በመድረኩ ጤና ሚኒስቴርን ወክለው የተገኙት ፕሮፌሰር ስለሺ ጋሮማ፤ የልብና ደም ሥር በሽታዎች ለሰው ልጅ ሞት ምክንያት ከሆኑ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች መካከል ዋናው ነው ብለዋል። ሕመሙን በቅድመ-ምርመራ እና በጊዜው በሚገኝ ጥራት ያለው ሕክምና መከላከል የሚቻል ቢሆንም፣ አሁንም ሰፊ የቤት ሥራ በመኖሩ ምክንያት አምራች የሰው ኃይልን እያሳጣ ይገኛል ነው ያሉት። የበሽታውን ተጽዕኖ ለመቀነስ ቅድመ-ምርመራን፣ ድንገተኛና ልዩ ሕክምናዎችን፣ ማገገሚያዎችን እንዲሁም ምርምርና ፈጠራን ያካተተ ጠንካራ የጤና ሥርዓት መገንባት እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ጉባኤው የአፍሪካውያንን የተቀናጀ ሥራ ለማጠናከር ከፍተኛ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት በዚሁ ዘርፍ ላይ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ጠቁመው በመሠረታዊ የጤና እንክብካቤ ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማስፋፋት፣ ልዩ የልብ ሕክምና ባለሙያዎች ሥልጠናን በመጨመር፣ በከፍተኛ ሕክምና ማዕከላት ማስፋፊያ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በሽታዎችን በመከላከል፣ አስፈላጊ መድኃኒቶችንና ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ በኩል ከሙያ ማኅበራት፣ ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከልማት አጋሮችና ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በትብብር እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የልብ ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት ዶክተር ናትናኤል ታዬ፤ የሕክምና መገልገያዎች እጥረት፣ የአገልግሎት አለመዳረስ እና የወረፋ ጥበቃ በዘርፉ ዋና ዋና ፈተናዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ሆኖም እነዚህን ፈተናዎች በመቋቋም ልዩ የሕክምና አገልግሎቶችን ማስፋፋት፣ የሀገር ውስጥ ሥልጠናና ምርምርን ማጠናከር፣ ዲጂታል የጤና ቴክኖሎጂዎችን መተግበርና ዘርፉን የሚቀይሩ አጋርነቶችን የመገንባት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል። የፓን-አፍሪካ የልብ ሕክምና ማኅበር ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ሀቢብ ጋምራ፤ በሽታውን ለመከላከል የሙያተኞች የእውቀትና ልምድ ልውውጥ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፣ ጉባኤው የጋራ መፍትሔዎችን ለማስቀመጥ ይረዳል ብለዋል።
የዛሬ ችግኞች የነገ የሀገር ትሩፋቶች
Aug 1, 2026 34
አረንጓዴ አሻራ በአፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ሀገር በቀል ምላሾች መካከል በዋናነት ይጠቀሳል። ኢኒሼቲቩ ሀገር በቀል እውቀት፣ የጋራ ተግባር እና መጠነ ሰፊ የማህበረሰብ ተሳትፎን በማቀናጀት ስኬታማ የሆነ ለዓለም የሚደርስና ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር የሚያሳይ ነው። አረንጓዴ አሻራ ከአካባቢ ጥበቃ ትሩፋቶቹ፣ የተራቆተ መሬትን ወደ ነበረበት ከመመለስ፣ የውሃ ሀብት አስተዳደርን በመጨመር እና የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ አንጻር ካለው ፋይዳ ባሻገር አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት ከውጭ መፍትሄ እስኪመጣ ከመጠበቅ በራሷ አቅም መፍትሄን ማመንጨት እንደምትችል የሚያሳይ ነው። የአረንጓዴ አሻራ ግብ ችግኝ መትከልና የአካባቢ ጥበቃ ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ግንባታ፣ የህዝብ አንድነት እና የኢኮኖሚ ልማት ማዕከል ማድረግ ሲሆን ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በቀጥታ ተሳታፊ እንዲሆኑና ለጋራ ብልጽግና በጋራ እንዲሰሩ እድል የፈጠረ ህዝባዊ ንቅናቄም ነው። ይህንኑ ሀገራዊ ኢኒሼቲቭ ይበልጥ ለማጠናከር “ተስፋን እንትከል!” በሚል መሪ ሀሳብ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አማካኝነት በይፋ ተጀምሯል። በዚህ ዓመት ብቻ ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን፤ ይህም ቀደም ሲል ተይዞ የነበረውን የ48 ቢሊዮን ችግኞች አጠቃላይ ግብ ወደ 65 ቢሊዮን ከፍ ያደረገ ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ነው። በተከታታይ በተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ስራም በ2010 ዓ.ም. 17 ነጥብ 2 በመቶ የነበረው የደን ሽፋን 2016 ዓ.ም. ላይ 23 ነጥብ 6 በመቶ ሊደርስ ችሏል። ለበርካታ አስርት ዓመታት የቆየውን የመሬት መራቆት መግታትም ተችሏል። በተጨማሪም ይህ ኢኒሼቲቭ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። የአረንጓዴ ዐሻራ ፋይዳ ግን የአፈርና ውኃ ጥበቃ እንዲሁም የደን ሽፋን መጨመር ብቻ አይደለም፤ የተፈጥሮ ደኖች መስፋፋታቸው ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የማር ምርትን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያድግና የስርዓተ-ምግብ መሻሻል እንዲረጋገጥ አድርጓል። አሁን ደግሞ የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ቀጠሮ ተይዟል። ይህ ታሪካዊ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላውን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት ውድ የሀገሬ ልጆች፤ በእነዚህ ቀናት አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ፣ በቁርጠኝነት እንድትነሱ እና በአንድነታችን የምናስመዘግበውን ድል እውን እንድናደርግ ጥሪዬን አቀርባለሁ። በጋራ ተስፋን እንትከል! ብለዋል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ፣ ዛፎችን የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ የተስፋ፣ የህብረት እና የሀገራዊ ህዳሴ ምልክት ነው። የዛሬዎቹ ችግኞች የነገዎቹ ደኖች፣ የነገዎቹ የውሃ ምንጮች እና የነገው ትውልድ ንጹህ አየር ናቸው። ይህ ንቅናቄ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት ያላትን ቁርጠኝነት ለዓለም ያሳየችበት፣ ዜጎቿም ለሀገራቸው እድገት በጋራ ሲቆሙ ምን ያህል ታላቅ ነገር መስራት እንደሚችሉ ያስመሰከሩበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። ዛሬ የተተከለው እያንዳንዱ ችግኝ ለነገዋ አረንጓዴ፣ ሰላማዊ እና የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚቀመጥ ጠንካራ የማዕዘን ድንጋይ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት የኢትዮጵያን የአየር ንብረት ዲፕሎማሲ በተግባር ያሳየ ነው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)
Aug 1, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት ሀገሪቱ የምትከተለውን የአየር ንብረት ዲፕሎማሲ በተግባር የሚያሳይ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቢሾፍቱ ከተማ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዷል። በመርሃ ግብሩ የጎረቤትና የሌሎች አፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች መሆኗን ማሳያ ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት እና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስተዋወቅን ጨምሮ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ሀገሪቱን በአየር ንብረት ዲፕሎማሲ ቀዳሚ ማድረጋቸውንም አብራርተዋል። ችግኝ ተከላው ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ያላትን ቁርጠኝነት በተጨባጭ ያሳየችበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ለቀጣናችንና ለአህጉራችን ለተሻለ የወደፊት ጊዜ፣ ለሰላምና ለአብሮነት ተስፋን እንተክላለን ሲሉም ተናግረዋል። ከሱዳን፣ ከኬንያ እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዲፕሎማቶች ጋር የተካሄደው የችግኝ ተከላ ልምድን ለማካፈል፣ ቀጣናዊ ትስስርንና ትብብርን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልጸዋል። የሚተከሉት ችግኞች ሲያድጉና ሲያፈሩ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዳላቸው የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር እንዲጸድቁና የሚፈለገውን ጥቅም እንዲሰጡ አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የአምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትና የቡና ወጪ ንግድን አሳድጓል
Aug 1, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የአምራች ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነትና የቡና ምርታማነትና ወጪ ንግድን በከፍተኛ በሁኔታ ማሳደጉን አምራቾችና ላኪዎች ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በሰጡት ማብራሪያ ሀገራዊ የሪፎርም ስራ ለውጭ ምንዛሬ ግኝት ስኬቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን መግለፃቸው ይታወሳል። ይህም በዘንድሮው ዓመት ከቡና ኤክስፖርት ብቻ 3 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ማስገኘት መቻሉን መግለፃቸውም እንዲሁ። የኦሮሚያ የቡና አቅራቢዎች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት እና የከብሬ ለኬ ቡና ላኪ ድርጅት ባለቤት ፈጠነ የኋላእሸት ለኢዜአ እንደገለጹት ከዚህ ቀደም በዘርፉ የነበሩ የፖሊሲ ክፍተቶች በቡና ምርትና ምርታማነት ላይ ተጽዕኖ ፈጥረው ቆይተዋል። ተግባራዊ የተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለዘርፉ ተዋናዮች መልካም እድል መፍጠሩን ጠቁመው ይህን ተከትሎም የቡና ኤክስፖርት በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍ እያለ መምጣቱን ገልጸዋል። የተደረገው ማሻሻያ በእሴት ሰንሰለቱ ላይ ያሉ ችግሮችን መለየት ማስቻሉን ይህም ቡና በቀላሉ ወደ ውጭ እንዲላክ ማድረጉን አስታውቀዋል። በተጨማሪም አሰራሮች ዲጂታላይዝ መደረጋቸው ዘርፉን ዘመናዊ እንዳደረገውና ለቡና ወጪ ንግድ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። ሪፎርሙን ተከትሎ በተሰሩ ስራዎች የቡና ምርታማነትና ጥራት በመጨመሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ መቻሉንም ገልጸዋል፡፡ በተለይም ባለፉት ሶስት ዓመታት የቡና ወጪ ንግድ በየዓመቱ በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍተኛ እድገት ማሳየቱን አብራርተዋል። በቀጣይም መንግስትና የዘርፉ ተዋናዮች ትብብራቸውን አጠናክረው ከቀጠሉ የወጪ ንግድ አፈፃፀምንና የዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነትን በዘላቂነት ማረጋገጥ እንደሚቻል አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ማሽነሪና መለዋወጫ አምራቾች ማህበር ፀሀፊ እና የፅዮን ኢንደስትሪያል ኢንጂነሪንግና ብረታ ብረት ኢንተርፕራይዝ ባለቤት ዮሃንስ ግርማ በበኩላቸው መንግስት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። በተለይም ተኪ ምርቶችን ለሚያመርቱና የወጪ ንግድ ኤክስፖርት ምርትን ለማሳደግ ለሚሰሩ አምራቾች ውጤታማ የሚያደርጉ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል። ለአምራች ዘርፉ በተሰጠው ትኩረትና እየተደረገ ባለው አጠቃላይ ድጋፍ የምርት ጥራትና ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ማጎልበት መቻሉንም ጨምረው አስታውቀዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እንደገለጹት፤ የኢንዱስትሪዎችን ችግር ከመለየት ጀምሮ በዘላቂነት ተወዳዳሪ ሊሆኑ የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቷል። የአምራች ኢንዱስትሪ ችግሮችን ለመፍታት የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በዘርፉ ከፍተኛ ውጤቶች መመዝገባቸውንም አመላክተዋል። ይህም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የፋይናንስ ማነቆ በመፍታት ቀደም ሲል 40 ቢሊየን ብር የነበረውን የብድር መጠን ወደ 115 ቢሊየን ብር ከፍ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በዚህም የኢንዱስትሪዎቻችን ተወዳዳሪነት፣ ምርታማነት፣ ትርፋማነትና የመስፋፋት ዕድል ከፍ እያለ መምጣቱን ገልጸዋል።
በወላይታ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል
Aug 1, 2026 67
ወላይታ ሶዶ ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ከ6 ሺህ 450 ሄክታር በላይ መሬት ላይ እንደሚተከሉ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዘማች ሶርሳ (ዶ/ር) በዞኑ ለዘንድሮ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቂ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። በዞኑ በሚገኙ ሁሉም የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ለመርሃ ግብሩ በተለዩ የመትከያ ቦታዎች ኅብረተሰቡን በንቃት ለማሳተፍ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ እየተሠራ ይገኛል። በመርሃ ግብሩም የፍራፍሬ፣ የቀርከሃ፣ የውበትና ጥላ፣ የጥምር ደን እንዲሁም ሌሎች ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን በመትከል ከ6 ሺህ 450 ሄክታር በላይ መሬት ይሸፈናል ብለዋል። ለዚህም የጉድጓድ ቁፋሮን ጨምሮ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት በሙሉ መጠናቀቁን የጠቆሙት ኃላፊው፤ በዕለቱ ከ828 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ተናግረዋል። ለዘመቻው መሳካትም በሳይንሳዊ ዘዴ የመትከያ ቦታዎች ልየታ መደረጉን በመጠቆም ሁሉም የአካባቢው ነዋሪዎች በነቂስ ወጥተው አሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ አቅርበዋል። «የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ከተጀመረ ወዲህ ገላጣ የነበሩ መሬቶች ለምተውና የደረቁ ምንጮች በመፍለቃቸው አርሰንም ሆነ አርብተን የተሻለ ኑሮ መምራት ጀምረናል» ያሉት ደግሞ በዞኑ ዳሞት ጋሌ ወረዳ የሻኪሾ ሾኔ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ገላነህ ቱማቶ ናቸው። ከዚህም የተነሳ ክረምቱ ከገባ ጀምሮ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች መትከል መጀመራቸውን አንስተው ሰኞ ዕለት ለሚካሄደው የአንድ ጀምበር ተከላም መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በወረዳው የቡጌ ቀበሌ አርሶ አደር ነጋ ጌቶ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም የተከሏቸው የፍራፍሬ እና ሌሎች ችግኞች ደርሰው በመሸጥ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ያነሳሉ። ዘንድሮም ከ100 በላይ ችግኞችን ለመትከል በግብርና ባለሙያ ድጋፍና ትምህርት መሠረት የጉድጓድ ቁፋሮ ማከናወናቸውን ጠቁመዋል።
ፖለቲካ
ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን አንድነት እና ክብር የሚያጸና ነው - የተለያዩ የእምነት ተቋማት አባቶች
Aug 1, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን አንድነት እና ክብር የሚያጸና እንደሚሆን ተመካካሪ የሃይማኖት አባቶች ገለጹ፡፡ ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ይገኛል። በጉባኤው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በመሰባሰብ በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት እየተመካከሩ ይገኛሉ። ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች፤ የምክክር ሂደቱ አሳታፊ፣ አካታችና ነፃ ሆኖ መካሄዱ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም፣ ሀገራዊ መግባባትና ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ተስፋ ሰጪ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ ተመካካሪዎች ማካከል መልዓከ ሕይወት አባ ወልደ ዮሐንስ ሰይፉ፤ በዚህ ምክክር ያልተወከለ ኢትዮጵያዊ የለም ብለዋል። ምክክሩ እርስ በእርስ ይበልጥ እንድንተዋወቅ እያደረገን ነው ያሉት መልዓከ ሕይወት፣ ሂደቱ አንዱ የሌላውን ሐሳብ ሳይነቅፍ፣ ፍጹም መከባበርና መተሳሰብ በሰፈነበት ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ይህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ፍቅር፣ ሰላምና ልማት የሚፈልግ መሆኑን ከመገንዘብ ባለፈ ሰላሟ የተጠበቀ፣ አረንጓዴና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ወሳኝ አዲስ ምዕራፍ መሆኑን አመልክተዋል። የምክክር ሂደቱ በአካታችነቱና አሳታፊነቱ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ተመካካሪ አብዱልመጂድ ጃፋር ናቸው። "ይዘን የመጣነው የሀገር ኃላፊነት ነው፤ በመሆኑም ስለ ሀገራችን ሰላም፣ ልማትና እድገት ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ ምክክር እያደረግን እንገኛለን" ሲሉም ተናግረዋል። ለሀገር በሚበጁ ጉዳዮች ላይ ተስፋ ሰጪ ውይይቶች እየተደረጉ መሆናቸውን ያመላከቱት ተመካካሪው፤ በሀገራችን የጋራ መግባባት ከተፈጠረ ሌላ የሚጎድል ነገር አለመኖሩን ጠቅሰዋል። ሐሳባቸውንም በነጻነት መግለጻቸውን በማንሳት፣ ከዚህ ምክክር በኋላ ሀገራችን በልማት ላይ ብቻ እንድታደርግ ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው ተመካካሪ ጻዲቁ አብዶ በበኩላቸው፤ ለአንድ ሀገር ዘላቂ መረጋጋትና ለጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ መሠረት በሚሆኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ በሰለጠነ መንገድ ሐሳብ እየተለዋወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ ልዩነቶችን በውይይት የመፍታት ባህልን የሚያጎለብትና ለትውልድ የሚሻገር ሰላምን የሚገነባ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሌላኛው ተመካካሪ አባ አማኑኤል ዮሴፍ በበኩላቸው፤ ምክክሩ ፍጹም የመደማመጥና ቤተሰባዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚያሻግሩ ሐሳቦች ተነስተው በነጻነት ምክክር እየተደረገባቸው እንደሚገኝም አመልክተዋል።
ከእውነት የራቀና ለትውልድ የማይበጅ የሴራ ትንተና ውጤቱ ጥፋት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 1, 2026 137
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ ከእውነት የራቀና ለዛሬም ሆነ ለመጪው ትውልድ የማይበጅ የሴራ ትንተና ውጤቱ ጥፋት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የኢትዮጵያ ህዝቦች የመዋሃድና አብሮ የመዝመት ታሪክ ቢኖራቸውም በዘመናት መካከል ስልጣን ሲመጣ አልጋ ሳይጸና በኃይል ስልጣን የመገዳደር ፍላጎት የሀገሪቱ ባህል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሁልጊዜም በኃይል ስልጣን ለመያዝ መሞከር የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እንደነበር አስታውሰው ለዚህም ከልጅ እያሱ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ከለውጡ በኃላ የተከሰተውን ሙከራ በማሳየነት አንስተዋል፡፡ በአማራ ክልል ተከስቶ የነበረው የሰኔ 15ቱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ግድያ ለየት የሚያደርገው በክልልና ከተማ ደረጃ ለመፈጸም የተሞከረ መሆኑ ነውም ብለዋል፡፡ ይህም በታሪክ እንደጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት መሆኑን ጠቁመው ይህ መጥፎ ክስተት የለውጥ ኃይል የሚባሉና ቢቆዩ ለሀገር ብዙ የሚያበረክቱ ሰዎችን ያሳጣ መሆኑን ገልጸዋል። ክስተቱ ይበልጥ የሚያሳዝነው ገዳይንም ሟችንም በጀግንነት ያወሳ በመሆኑ ታሪክን እያንሻፈፉ በፈለጉት መንገድ በማቆየት ትልቅ የትርክት ስብራት የፈጠረ እንደሆነም ነው የተናገሩት፡፡ ከመልካምም ከመጥፎም ታሪክ መማር ያስፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ታሪክን እየመረጡና እያንሻፈፉ ማቆየት የነገውን ትውልድ ዋጋ ያስከፍላል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡ አሁን ያለው የኢትዮጵያ ታሪክም የተንሸዋረረ የፖለቲካ ትርክት ውጤት መሆኑን በመጠቆም በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ታሪክ የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀሚያ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ከእውነት የራቀና ለዛሬም ሆነ ለነገ የማይበጅ የሴራ ትንተና ጥፋት እንደሚያመጣም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገለጹት፡፡
ለውጥ የአንድ ሰሞን ድግስ ሳይሆን ሂደት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 1, 2026 119
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ ለውጥ የአንድ ሰሞን ድግስ ሳይሆን ሂደት በመሆኑ በዚህ ውስጥ ጉዳዮች ሊቀያየሩ እንደሚችሉ መገንዘብ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡ በቆይታቸውም ለውጡንና የዳያስፖራዎችን ሚና በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፤ ለውጡን በመደገፍና ባለመደገፍ ጎራ የመቀያየር ሁኔታ በዳያስፖራዎችም ሆነ አልፎ አልፎ በሀገር ውስጥ ባሉ ግለሰቦችም ይታይ እንደነበር አንስተዋል፡፡ ለዚህም ሶስት ጉዳዮችን በምክንያትነት ያነሱ ሲሆን ግለሰቦች የነበራቸው የተሳሳተ ስሌት የመጀመርያው መሆኑን ጠቁመዋል። አንዳንድ ግለሰቦች የለውጡ ባለቤት እንደሆኑንና ለውጡ እኔ በማስበው መንገድ መሄድ አለበት የሚል እምነት ያላቸው ግለሰቦች ሃሳብ የተጋባባቸው ናቸው ብለዋል፡፡ ለውጡ የብዙ ሰዎች ጥረትና በርካቶች ዋጋ የከፈሉበት በመሆኑ በማስተባበር የሚመራ እንጂ የግለሰቦችን ፍላጎት ለማሳካት የሚፈጸም አለመሆኑን ሲረዱ የጎራ ለውጥ የሚያሳዩ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ በተመሳሳይ ለርካሽ ዓላማ የሚቃወሙ ግለሰቦች መኖራቸውን አንስተው እነዚህም ከማህበረዊ ሚዲያ ንግድና ከተለያዩ ሀገራት ጥገኝነት ለመጠየቅ በሚደረግ ሙከራ ምክንያት የሚቃወሙና፣ መቃረን ብቸኛ መንገድ ነው ብለው የሚያምኑ ግለሰቦች ናቸው ብለዋል፡፡ እነዚህ ሰዎች ወደ ሀገር ሲመለሱ ለውጡን የሚያደንቁ መሆናቸውንም አብራርተዋል፡፡ እውነተኛ ጥያቄ ያላቸውና በበቂ ደረጃ ምላሽ ያላገኙ ሲመስላቸው የሚቃወሙ ግለሰቦች መኖራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ የእኛም ድክመት ሊሆን ይችላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ለውጥ ዳር በመቆም ብቻ አይሳካም መሳተፍ ይፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እውነተኛ ጥያቄ ያላቸው ግለሰቦች ቀረብ ብለው ይጠይቁ፣ ለውጡንም ይመልከቱ ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በተሳሳተ ስሌት ውጤቱን የገመቱ ሰዎች የኢትዮጵያንና የዘመኑን ነባራዊ ሁኔታ ሊገነዘቡ እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት፡፡ ለጊዜያዊ ችግር ሲሉ ጫናን መቋቋም የሚሳናቸው ግለሰቦችም ችግር በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚፈታ ስላልሆነ ለርካሽ ጥቅም ሲባል ከቁምነገር መጉደል አይሁንባችሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ታሪክ መስራት ካልተቻለ ከታሪክ ጎን መቆም እንጂ ለወቅታዊ ችግር ሲባል አቋም በማጣትና በመወላወል የሀገርን ጥቅም ማሳጣት አይገባም ብለዋል፡፡ ውጤት እና ማገናዘብ እስካለ ድረስ የሰው ልጅ እውነታው እየተገለጠለት መሄዱ እንደማይቀርም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተናገሩት፡፡
አካታች በሆነው ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት እየመከርን ነው
Jul 31, 2026 361
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ) ፦አካታች በሆነው ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት እየመከርን ነው ሲሉ ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ስምንት የምክክር አጀንዳዎችን በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የምክክር ጉባዔ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው ምክክር አራት ሺህ ተመካካሪዎች እየመከሩ ይገኛሉ። በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ ያሉ ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ያስችላል። ሂደቱ ሁሉም ዜጋ ለሀገሩ የድርሻውን የሚያበረክትበት አውድ የፈጠረ በመሆኑ፣ ለሀገር ግንባታ የሚረዱ ገንቢ ሀሳቦችን እያንሸራሸሩበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ተመካካሪ ወጣት ከበደች ኢዶሳ በሰጠችው አስተያየት፤ የምክክሩ ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን በምክክር ፈተው የተሻለች ሀገርን ለመገንባት የሚያስችላቸው ታሪካዊ ዕድል መሆኑን ገልጻለች፡፡ ምክክሩ ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን ያረጋገጠ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያን ያሻግራል ተብሎ የሚታመንባቸው ሀሳቦች ሁሉ እየተንጸባረቁበት የሚገኝ መሆኑን ተናግራለች፡፡ ምክክሩ በዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ ትልቅ አሻራ እንደሚኖረው ጠቅሳ ሁሉም አካላት እየተሳተፉበት የሚገኝ ምክክር እንደመሆኑ ለችግሮች ትልቅ መፍትሔ መሆኑንም ጠቅሳለች፡፡ ወጣት መንግስቱ ጉሚ በበኩሉ፤ እስካሁን ያለው የምክክር ሂደት ባማረ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተናግሯል። ምክክሩ ሁሉም ሰው የሚፈልገውን ሀሳብ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የሚያነሳበትና በነፃነት የሚወያይበት መድረክ መሆኑንም ጠቅሷል። ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ ወደ ተሻለ ደረጃ ያሸጋግራል ብሎ እንደሚያምን ጠቅሶ ይህም የሀገሪቱን ስብራት የሚጠግን መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ምክክሩ ሁሉንም ብሔሮችና ብሔረሰቦች ያካተተና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን የጠቀሰው ይይ ቤምሪክ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን በማጥበብና ወደ አንድነት በሚመጣ መንገድ እየተመካከሩ መሆኑን ጠቅሶ፤ ይህም የተጀመሩ የልማት ስራዎች በተሻለ ሁኔታ እንዲከናወኑ እንደሚያስችል ተናግሯል። ወጣት ደነቀ ዳጮ በበኩሉ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ባካተተ መልኩ እየተከናወነ ነው ብሏል፡፡ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባት የተፈጠረባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ተስፋ እንዳለው ተናግሯል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና አንድነት ትልቅ ተስፋ የሰነቀ ነው -ወጣት ተመካካሪዎች
Jul 31, 2026 325
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ) ፦ሀገራዊ ምክክር ጉባዔው የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላምና አንድነትን ለማጠናከር ትልቅ ተስፋ መሆኑን በጉባኤው እየተሳተፉ የሚገኙ ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ነው። በጉባኤው በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እየተመካከሩ ይገኛሉ። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ዕድሉ ከበደ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት፣ የምክክር ሂደቱ ከታችኛው የውይይት እርከን ጀምሮ ደረጃውን ጠብቆ ውጤታማ በሆነ መልኩ በመግባባት መንፈስ እየተካሄደ ነው ብሏል። ሂደቱ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ያካተተና በነጻነት ሀሳብ የሚንጸባረቅበት መሆኑን የገለጸው ወጣት ዕድሉ፤ በውይይቱም የጋራ ሀገርን ማስቀደም እና የሌላውን ሀሳብ ማዳመጥ ማዕከል መደረጉን ገልጿል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ወጣት ኢስራ አብዱላሂ በበኩሏ፤ የምክክር መድረኩ ሴቶችን፣ ወጣቶችንና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ያካተተ መሆኑን አንስታለች። ተሳታፊዎች እርስ በእርስ በመደጋገፍና በመደማመጥ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም መፍትሔ እንደሚያመጡ እምነቷን ተናግራለች። ተመካካሪ ወጣት ገለታ ገቢሳ በበኩሉ፤ ኢትዮጵያውያን ተደማምጠው በነጻነትና በሀሳብ ብልጫ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከራቸው የተሰማውን ደስታ ገልጿል። በምክክሩ የተለያዩ ሃይማኖቶችና የህብረተሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን አስታውሶ፤ ምክክሩ ለሀገር ሰላምና እድገት መረጋገጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ተናግሯል።
የምክክር ጉባኤው የጋራ መግባባትን በማጠናከር ለሕዝብ አብሮነትና ዘላቂ የሀገር ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው
Jul 31, 2026 327
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የጋራ መግባባትን በማጠናከር ለሕዝብ አብሮነትና ዘላቂ የሀገር ግንባታ መሰረት የሚጥል መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ተመካካሪና የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) አባል ሙሐሙድ መሐመድ ሀሰን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ይፋ የተጀመረው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ነው። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። የጉባኤው ተመካካሪ ሙሐሙድ መሐመድ ሀሰን ለኢዜአ እንዳሉት፤ በሀገሪቱ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ አጀንዳዎች ዙሪያ ገንቢና ግልጽ ምክክር እያደረጉ ነው። ተመካካሪዎችም የኢትዮጵያን ብዝኅነት፣ ሕብረ-ብሔራዊ እሴቶችና የጋራ ሀገራዊ ጥቅሞችን በሚያንጸባርቁ ሃሳቦች ላይ እንዲመክሩ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። የሚንጸባረቁ ሃሳቦችም የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል የሚያስችል የጋራ መግባባት እንዲፈጠር ወሳኝ ሚና እንደሚኖራቸው ተናግረዋል። በተጨማሪም የምክክር ሂደቱ አካታችና አሳታፊ በመሆኑ በተለያዩ ሃሳቦች መካከል በመተማመንና በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ምክክር እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የጋራ መግባባትን በማጠናከር ለሕዝብ አብሮነትና ለዘላቂ ሀገር ግንባታ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። ሀገራዊ አለመግባባቶችን በኃይል ለመፍታት መሞከር ዘላቂ መፍትሔ የማያማጣና አዋጭ ያልሆነ አካሄድ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በዚህም በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ ምክክር በሀገራዊ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ወሳኝ መንገድ መሆኑን አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ደረጃ እያካሄደች ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ጭምር ተምሳሌትና ተሞክሮ የሚሆን ውጤት እንደሚያስገኝ እምነታቸውን ገልጸዋል።
ለሀገራዊ ችግሮች በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ለመስጠት እየመከርን ነው
Jul 31, 2026 327
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሀገራዊ ችግሮች ላይ በመመካከር በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ለመስጠት እየተመካከሩ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ የጀመረው የኢትዮጵያ ዋናው የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲሱ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ነው። በጉባኤው በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እየተመካከሩ ይገኛሉ። ከተመካካሪ ምሁራን መካከል የታሪክና የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ኢንጂነር አልአዛር ዓባይነህ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በአንድ መድረክ ተሰባስበው በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መመካከራቸው ለሀገራዊ መግባባት ግንባታ ትልቅ ዕድል ነው። በጉባኤው በተመካካሪዎች መካከል ግልጽ፣ አሳታፊና አንዱ የሌላውን ሃሳብ በነጻነት የሚያዳምጥበትና የሚረዳበት የውይይት አካባቢ መፈጠሩንም ገልጸዋል። በተመካካሪዎች መካከል ያለገደብ የሚንጸባረቁ ሃሳቦች ሀገሪቱን በተሻለ መልኩ የሚቀርጹ የጋራ መግባባቶችን ለመገንባት ወሳኝ መሆናቸውንም አስረድተዋል። ከዚህ ቀደም በተፈጠሩ የተዛቡ ትርክቶችና አለመግባባቶች ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ስትፈተን መቆየቷን ያስታወሱት ኢንጂነር አልአዛር፤ የሀገሪቱን ውስብስብ ቋጠሮዎች ለመፍታት ከምክክር ውጭ ሌላ አማራጭ እንደሌለ ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው በሀገራዊ መግባባት የጸናች ኢትዮጵያን ለመገንባትና ለመጪው ትውልድ ብሩህ መሠረት ለመጣል ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑንም ጠቁመዋል። በጉባኤው ላይ ለሀገር የሚጠቅም ሃሳብ በማበርከት የታሪኩ አካል በመሆናቸው ኩራት እንደሚሰማቸውም ገልጸዋል። ሌላኛው ተመካካሪ አባት አቶ ዘለቀ ዘውዴ በበኩላቸው፥ በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ በመግባባትና በመከባበር መንፈስ ውይይት እያካሄዱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተመካካሪዎች የሚያንጸባርቋቸው ሃሳቦች የሀገርን አንድነትና የሕዝብን አብሮነት በማጠናከር ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስረከብ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም ገልጸዋል። በምክክር ጉባኤው ላይ እየተመከረባቸው ያሉት የሕዝብ አጀንዳዎች የኢትዮጵያን ሰላም፣ አንድነትና መረጋጋት ለማጠናከር ወሳኝ መሸጋገሪያ እንደሚሆኑም አመልክተዋል። የምክክር ጉባኤው በግልጽ፣ አካታችና አሳታፊ መንፈስ ከተጀመረበት ዕለት አንስቶ ለሀገር በሚበጅ መልኩ በስኬት እየተካሄደ ነው ያሉት ደግሞ ተመካካሪ ደማይ ኮክ ናቸው። ተመካካሪዎች በንቃት እየተሳተፉ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ጥልቅና ሰፊ ውይይቶች እያካሄዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የምክክሩ አሳታፊነትና አካታችነት የሚደነቅ መሆኑን የጠቀሱት ደማይ ኮክ፤ ከመድረኩ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ለዘላቂ ልማትና ለሰላም መስፈን መሠረት የሚሆኑ ጠቃሚ ሃሳቦች እየፈለቁ መሆኑን ገልጸዋል።
በምክክሩ ኢትዮጵያን ወደፊት የሚያራምዱ ሀሳቦች እየተንጸባረቁ ነው-ተመካካሪ
Jul 31, 2026 401
በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያን ወደፊት የሚያራምዱ ሀሳቦች እየተንጸባረቁ ይገኛሉ ሲሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አማካሪ ኮሚቴ አባል መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) ገለጹ። ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ይገኛል። በዚህም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። መብራቱ አለሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በምክክሩ ላይ ኢትዮጵያን ወደፊት ሊያራምዱ እና የታሪክ ቁስሎቻችንን ሊፈቱ የሚችሉ ሀሳቦች እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ምክክሩ አካታችነቱን የጠበቀ መሆኑን ገልጸው፤ተመካካሪዎችም ሀሳባቸውን በነጻነት እያቀረቡ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ ተደርጎ የማያውቅ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ተናግረዋል። ምክክሩ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ትልቅ ዕድል መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም የሚያስማሙን ጉዳዮችን የጋራ እያደረግን መቀጠል ይገባናል ብለዋል። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በሀገራቸው ጉዳይ እየመከሩ ነው፤ ይህም በፖለቲካ ምህዳሩ ምክክርን ባህል እያደረግን መምጣታችንን የሚያሳይ ነው ብለዋል። በዚህም የእኔ ሀሳብ ሁሌ ትክክል ነው የሚለውን እሳቤ በመተው በመመካከርና በመግባባት ሀገርን የሚያሻግሩ ሀሳቦችን እያንጸባረቅን ነው ብለዋል። በመሆኑም የምክክር ጉባኤው ለግጭት መንስኤ የሆኑ፣ዘላቂ ሰላምን፣ልማትን የሚያደናቅፉ ችግሮችን በመፍታት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል።
ፖለቲካ
ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን አንድነት እና ክብር የሚያጸና ነው - የተለያዩ የእምነት ተቋማት አባቶች
Aug 1, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን አንድነት እና ክብር የሚያጸና እንደሚሆን ተመካካሪ የሃይማኖት አባቶች ገለጹ፡፡ ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ይገኛል። በጉባኤው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በመሰባሰብ በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት እየተመካከሩ ይገኛሉ። ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች፤ የምክክር ሂደቱ አሳታፊ፣ አካታችና ነፃ ሆኖ መካሄዱ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም፣ ሀገራዊ መግባባትና ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ተስፋ ሰጪ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ ተመካካሪዎች ማካከል መልዓከ ሕይወት አባ ወልደ ዮሐንስ ሰይፉ፤ በዚህ ምክክር ያልተወከለ ኢትዮጵያዊ የለም ብለዋል። ምክክሩ እርስ በእርስ ይበልጥ እንድንተዋወቅ እያደረገን ነው ያሉት መልዓከ ሕይወት፣ ሂደቱ አንዱ የሌላውን ሐሳብ ሳይነቅፍ፣ ፍጹም መከባበርና መተሳሰብ በሰፈነበት ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ይህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ፍቅር፣ ሰላምና ልማት የሚፈልግ መሆኑን ከመገንዘብ ባለፈ ሰላሟ የተጠበቀ፣ አረንጓዴና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ወሳኝ አዲስ ምዕራፍ መሆኑን አመልክተዋል። የምክክር ሂደቱ በአካታችነቱና አሳታፊነቱ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ተመካካሪ አብዱልመጂድ ጃፋር ናቸው። "ይዘን የመጣነው የሀገር ኃላፊነት ነው፤ በመሆኑም ስለ ሀገራችን ሰላም፣ ልማትና እድገት ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ ምክክር እያደረግን እንገኛለን" ሲሉም ተናግረዋል። ለሀገር በሚበጁ ጉዳዮች ላይ ተስፋ ሰጪ ውይይቶች እየተደረጉ መሆናቸውን ያመላከቱት ተመካካሪው፤ በሀገራችን የጋራ መግባባት ከተፈጠረ ሌላ የሚጎድል ነገር አለመኖሩን ጠቅሰዋል። ሐሳባቸውንም በነጻነት መግለጻቸውን በማንሳት፣ ከዚህ ምክክር በኋላ ሀገራችን በልማት ላይ ብቻ እንድታደርግ ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው ተመካካሪ ጻዲቁ አብዶ በበኩላቸው፤ ለአንድ ሀገር ዘላቂ መረጋጋትና ለጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ መሠረት በሚሆኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ በሰለጠነ መንገድ ሐሳብ እየተለዋወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ ልዩነቶችን በውይይት የመፍታት ባህልን የሚያጎለብትና ለትውልድ የሚሻገር ሰላምን የሚገነባ መሆኑንም ጠቁመዋል። ሌላኛው ተመካካሪ አባ አማኑኤል ዮሴፍ በበኩላቸው፤ ምክክሩ ፍጹም የመደማመጥና ቤተሰባዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚያሻግሩ ሐሳቦች ተነስተው በነጻነት ምክክር እየተደረገባቸው እንደሚገኝም አመልክተዋል።
ከእውነት የራቀና ለትውልድ የማይበጅ የሴራ ትንተና ውጤቱ ጥፋት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 1, 2026 137
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ ከእውነት የራቀና ለዛሬም ሆነ ለመጪው ትውልድ የማይበጅ የሴራ ትንተና ውጤቱ ጥፋት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የኢትዮጵያ ህዝቦች የመዋሃድና አብሮ የመዝመት ታሪክ ቢኖራቸውም በዘመናት መካከል ስልጣን ሲመጣ አልጋ ሳይጸና በኃይል ስልጣን የመገዳደር ፍላጎት የሀገሪቱ ባህል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሁልጊዜም በኃይል ስልጣን ለመያዝ መሞከር የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እንደነበር አስታውሰው ለዚህም ከልጅ እያሱ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ከለውጡ በኃላ የተከሰተውን ሙከራ በማሳየነት አንስተዋል፡፡ በአማራ ክልል ተከስቶ የነበረው የሰኔ 15ቱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ግድያ ለየት የሚያደርገው በክልልና ከተማ ደረጃ ለመፈጸም የተሞከረ መሆኑ ነውም ብለዋል፡፡ ይህም በታሪክ እንደጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት መሆኑን ጠቁመው ይህ መጥፎ ክስተት የለውጥ ኃይል የሚባሉና ቢቆዩ ለሀገር ብዙ የሚያበረክቱ ሰዎችን ያሳጣ መሆኑን ገልጸዋል። ክስተቱ ይበልጥ የሚያሳዝነው ገዳይንም ሟችንም በጀግንነት ያወሳ በመሆኑ ታሪክን እያንሻፈፉ በፈለጉት መንገድ በማቆየት ትልቅ የትርክት ስብራት የፈጠረ እንደሆነም ነው የተናገሩት፡፡ ከመልካምም ከመጥፎም ታሪክ መማር ያስፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ታሪክን እየመረጡና እያንሻፈፉ ማቆየት የነገውን ትውልድ ዋጋ ያስከፍላል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡ አሁን ያለው የኢትዮጵያ ታሪክም የተንሸዋረረ የፖለቲካ ትርክት ውጤት መሆኑን በመጠቆም በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ታሪክ የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀሚያ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ከእውነት የራቀና ለዛሬም ሆነ ለነገ የማይበጅ የሴራ ትንተና ጥፋት እንደሚያመጣም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገለጹት፡፡
ለውጥ የአንድ ሰሞን ድግስ ሳይሆን ሂደት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 1, 2026 119
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ ለውጥ የአንድ ሰሞን ድግስ ሳይሆን ሂደት በመሆኑ በዚህ ውስጥ ጉዳዮች ሊቀያየሩ እንደሚችሉ መገንዘብ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡ በቆይታቸውም ለውጡንና የዳያስፖራዎችን ሚና በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፤ ለውጡን በመደገፍና ባለመደገፍ ጎራ የመቀያየር ሁኔታ በዳያስፖራዎችም ሆነ አልፎ አልፎ በሀገር ውስጥ ባሉ ግለሰቦችም ይታይ እንደነበር አንስተዋል፡፡ ለዚህም ሶስት ጉዳዮችን በምክንያትነት ያነሱ ሲሆን ግለሰቦች የነበራቸው የተሳሳተ ስሌት የመጀመርያው መሆኑን ጠቁመዋል። አንዳንድ ግለሰቦች የለውጡ ባለቤት እንደሆኑንና ለውጡ እኔ በማስበው መንገድ መሄድ አለበት የሚል እምነት ያላቸው ግለሰቦች ሃሳብ የተጋባባቸው ናቸው ብለዋል፡፡ ለውጡ የብዙ ሰዎች ጥረትና በርካቶች ዋጋ የከፈሉበት በመሆኑ በማስተባበር የሚመራ እንጂ የግለሰቦችን ፍላጎት ለማሳካት የሚፈጸም አለመሆኑን ሲረዱ የጎራ ለውጥ የሚያሳዩ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ በተመሳሳይ ለርካሽ ዓላማ የሚቃወሙ ግለሰቦች መኖራቸውን አንስተው እነዚህም ከማህበረዊ ሚዲያ ንግድና ከተለያዩ ሀገራት ጥገኝነት ለመጠየቅ በሚደረግ ሙከራ ምክንያት የሚቃወሙና፣ መቃረን ብቸኛ መንገድ ነው ብለው የሚያምኑ ግለሰቦች ናቸው ብለዋል፡፡ እነዚህ ሰዎች ወደ ሀገር ሲመለሱ ለውጡን የሚያደንቁ መሆናቸውንም አብራርተዋል፡፡ እውነተኛ ጥያቄ ያላቸውና በበቂ ደረጃ ምላሽ ያላገኙ ሲመስላቸው የሚቃወሙ ግለሰቦች መኖራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ የእኛም ድክመት ሊሆን ይችላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ለውጥ ዳር በመቆም ብቻ አይሳካም መሳተፍ ይፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እውነተኛ ጥያቄ ያላቸው ግለሰቦች ቀረብ ብለው ይጠይቁ፣ ለውጡንም ይመልከቱ ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በተሳሳተ ስሌት ውጤቱን የገመቱ ሰዎች የኢትዮጵያንና የዘመኑን ነባራዊ ሁኔታ ሊገነዘቡ እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት፡፡ ለጊዜያዊ ችግር ሲሉ ጫናን መቋቋም የሚሳናቸው ግለሰቦችም ችግር በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚፈታ ስላልሆነ ለርካሽ ጥቅም ሲባል ከቁምነገር መጉደል አይሁንባችሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ታሪክ መስራት ካልተቻለ ከታሪክ ጎን መቆም እንጂ ለወቅታዊ ችግር ሲባል አቋም በማጣትና በመወላወል የሀገርን ጥቅም ማሳጣት አይገባም ብለዋል፡፡ ውጤት እና ማገናዘብ እስካለ ድረስ የሰው ልጅ እውነታው እየተገለጠለት መሄዱ እንደማይቀርም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተናገሩት፡፡
አካታች በሆነው ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት እየመከርን ነው
Jul 31, 2026 361
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ) ፦አካታች በሆነው ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት እየመከርን ነው ሲሉ ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ስምንት የምክክር አጀንዳዎችን በመለየት ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የምክክር ጉባዔ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው ምክክር አራት ሺህ ተመካካሪዎች እየመከሩ ይገኛሉ። በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ ያሉ ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ያስችላል። ሂደቱ ሁሉም ዜጋ ለሀገሩ የድርሻውን የሚያበረክትበት አውድ የፈጠረ በመሆኑ፣ ለሀገር ግንባታ የሚረዱ ገንቢ ሀሳቦችን እያንሸራሸሩበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ተመካካሪ ወጣት ከበደች ኢዶሳ በሰጠችው አስተያየት፤ የምክክሩ ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን በምክክር ፈተው የተሻለች ሀገርን ለመገንባት የሚያስችላቸው ታሪካዊ ዕድል መሆኑን ገልጻለች፡፡ ምክክሩ ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን ያረጋገጠ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያን ያሻግራል ተብሎ የሚታመንባቸው ሀሳቦች ሁሉ እየተንጸባረቁበት የሚገኝ መሆኑን ተናግራለች፡፡ ምክክሩ በዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ ትልቅ አሻራ እንደሚኖረው ጠቅሳ ሁሉም አካላት እየተሳተፉበት የሚገኝ ምክክር እንደመሆኑ ለችግሮች ትልቅ መፍትሔ መሆኑንም ጠቅሳለች፡፡ ወጣት መንግስቱ ጉሚ በበኩሉ፤ እስካሁን ያለው የምክክር ሂደት ባማረ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተናግሯል። ምክክሩ ሁሉም ሰው የሚፈልገውን ሀሳብ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የሚያነሳበትና በነፃነት የሚወያይበት መድረክ መሆኑንም ጠቅሷል። ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ ወደ ተሻለ ደረጃ ያሸጋግራል ብሎ እንደሚያምን ጠቅሶ ይህም የሀገሪቱን ስብራት የሚጠግን መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ምክክሩ ሁሉንም ብሔሮችና ብሔረሰቦች ያካተተና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን የጠቀሰው ይይ ቤምሪክ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን በማጥበብና ወደ አንድነት በሚመጣ መንገድ እየተመካከሩ መሆኑን ጠቅሶ፤ ይህም የተጀመሩ የልማት ስራዎች በተሻለ ሁኔታ እንዲከናወኑ እንደሚያስችል ተናግሯል። ወጣት ደነቀ ዳጮ በበኩሉ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ባካተተ መልኩ እየተከናወነ ነው ብሏል፡፡ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባት የተፈጠረባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ተስፋ እንዳለው ተናግሯል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና አንድነት ትልቅ ተስፋ የሰነቀ ነው -ወጣት ተመካካሪዎች
Jul 31, 2026 325
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ) ፦ሀገራዊ ምክክር ጉባዔው የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላምና አንድነትን ለማጠናከር ትልቅ ተስፋ መሆኑን በጉባኤው እየተሳተፉ የሚገኙ ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ነው። በጉባኤው በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እየተመካከሩ ይገኛሉ። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ዕድሉ ከበደ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት፣ የምክክር ሂደቱ ከታችኛው የውይይት እርከን ጀምሮ ደረጃውን ጠብቆ ውጤታማ በሆነ መልኩ በመግባባት መንፈስ እየተካሄደ ነው ብሏል። ሂደቱ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ያካተተና በነጻነት ሀሳብ የሚንጸባረቅበት መሆኑን የገለጸው ወጣት ዕድሉ፤ በውይይቱም የጋራ ሀገርን ማስቀደም እና የሌላውን ሀሳብ ማዳመጥ ማዕከል መደረጉን ገልጿል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ወጣት ኢስራ አብዱላሂ በበኩሏ፤ የምክክር መድረኩ ሴቶችን፣ ወጣቶችንና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ያካተተ መሆኑን አንስታለች። ተሳታፊዎች እርስ በእርስ በመደጋገፍና በመደማመጥ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም መፍትሔ እንደሚያመጡ እምነቷን ተናግራለች። ተመካካሪ ወጣት ገለታ ገቢሳ በበኩሉ፤ ኢትዮጵያውያን ተደማምጠው በነጻነትና በሀሳብ ብልጫ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከራቸው የተሰማውን ደስታ ገልጿል። በምክክሩ የተለያዩ ሃይማኖቶችና የህብረተሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን አስታውሶ፤ ምክክሩ ለሀገር ሰላምና እድገት መረጋገጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ተናግሯል።
የምክክር ጉባኤው የጋራ መግባባትን በማጠናከር ለሕዝብ አብሮነትና ዘላቂ የሀገር ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው
Jul 31, 2026 327
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የጋራ መግባባትን በማጠናከር ለሕዝብ አብሮነትና ዘላቂ የሀገር ግንባታ መሰረት የሚጥል መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ተመካካሪና የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) አባል ሙሐሙድ መሐመድ ሀሰን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ይፋ የተጀመረው የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ነው። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። የጉባኤው ተመካካሪ ሙሐሙድ መሐመድ ሀሰን ለኢዜአ እንዳሉት፤ በሀገሪቱ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ አጀንዳዎች ዙሪያ ገንቢና ግልጽ ምክክር እያደረጉ ነው። ተመካካሪዎችም የኢትዮጵያን ብዝኅነት፣ ሕብረ-ብሔራዊ እሴቶችና የጋራ ሀገራዊ ጥቅሞችን በሚያንጸባርቁ ሃሳቦች ላይ እንዲመክሩ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። የሚንጸባረቁ ሃሳቦችም የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል የሚያስችል የጋራ መግባባት እንዲፈጠር ወሳኝ ሚና እንደሚኖራቸው ተናግረዋል። በተጨማሪም የምክክር ሂደቱ አካታችና አሳታፊ በመሆኑ በተለያዩ ሃሳቦች መካከል በመተማመንና በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ምክክር እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የጋራ መግባባትን በማጠናከር ለሕዝብ አብሮነትና ለዘላቂ ሀገር ግንባታ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። ሀገራዊ አለመግባባቶችን በኃይል ለመፍታት መሞከር ዘላቂ መፍትሔ የማያማጣና አዋጭ ያልሆነ አካሄድ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በዚህም በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ ምክክር በሀገራዊ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ወሳኝ መንገድ መሆኑን አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ደረጃ እያካሄደች ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ጭምር ተምሳሌትና ተሞክሮ የሚሆን ውጤት እንደሚያስገኝ እምነታቸውን ገልጸዋል።
ለሀገራዊ ችግሮች በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ለመስጠት እየመከርን ነው
Jul 31, 2026 327
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሀገራዊ ችግሮች ላይ በመመካከር በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ለመስጠት እየተመካከሩ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ የጀመረው የኢትዮጵያ ዋናው የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲሱ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ነው። በጉባኤው በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እየተመካከሩ ይገኛሉ። ከተመካካሪ ምሁራን መካከል የታሪክና የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ኢንጂነር አልአዛር ዓባይነህ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በአንድ መድረክ ተሰባስበው በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መመካከራቸው ለሀገራዊ መግባባት ግንባታ ትልቅ ዕድል ነው። በጉባኤው በተመካካሪዎች መካከል ግልጽ፣ አሳታፊና አንዱ የሌላውን ሃሳብ በነጻነት የሚያዳምጥበትና የሚረዳበት የውይይት አካባቢ መፈጠሩንም ገልጸዋል። በተመካካሪዎች መካከል ያለገደብ የሚንጸባረቁ ሃሳቦች ሀገሪቱን በተሻለ መልኩ የሚቀርጹ የጋራ መግባባቶችን ለመገንባት ወሳኝ መሆናቸውንም አስረድተዋል። ከዚህ ቀደም በተፈጠሩ የተዛቡ ትርክቶችና አለመግባባቶች ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ስትፈተን መቆየቷን ያስታወሱት ኢንጂነር አልአዛር፤ የሀገሪቱን ውስብስብ ቋጠሮዎች ለመፍታት ከምክክር ውጭ ሌላ አማራጭ እንደሌለ ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው በሀገራዊ መግባባት የጸናች ኢትዮጵያን ለመገንባትና ለመጪው ትውልድ ብሩህ መሠረት ለመጣል ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑንም ጠቁመዋል። በጉባኤው ላይ ለሀገር የሚጠቅም ሃሳብ በማበርከት የታሪኩ አካል በመሆናቸው ኩራት እንደሚሰማቸውም ገልጸዋል። ሌላኛው ተመካካሪ አባት አቶ ዘለቀ ዘውዴ በበኩላቸው፥ በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ በመግባባትና በመከባበር መንፈስ ውይይት እያካሄዱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተመካካሪዎች የሚያንጸባርቋቸው ሃሳቦች የሀገርን አንድነትና የሕዝብን አብሮነት በማጠናከር ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስረከብ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም ገልጸዋል። በምክክር ጉባኤው ላይ እየተመከረባቸው ያሉት የሕዝብ አጀንዳዎች የኢትዮጵያን ሰላም፣ አንድነትና መረጋጋት ለማጠናከር ወሳኝ መሸጋገሪያ እንደሚሆኑም አመልክተዋል። የምክክር ጉባኤው በግልጽ፣ አካታችና አሳታፊ መንፈስ ከተጀመረበት ዕለት አንስቶ ለሀገር በሚበጅ መልኩ በስኬት እየተካሄደ ነው ያሉት ደግሞ ተመካካሪ ደማይ ኮክ ናቸው። ተመካካሪዎች በንቃት እየተሳተፉ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ጥልቅና ሰፊ ውይይቶች እያካሄዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የምክክሩ አሳታፊነትና አካታችነት የሚደነቅ መሆኑን የጠቀሱት ደማይ ኮክ፤ ከመድረኩ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ለዘላቂ ልማትና ለሰላም መስፈን መሠረት የሚሆኑ ጠቃሚ ሃሳቦች እየፈለቁ መሆኑን ገልጸዋል።
በምክክሩ ኢትዮጵያን ወደፊት የሚያራምዱ ሀሳቦች እየተንጸባረቁ ነው-ተመካካሪ
Jul 31, 2026 401
በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያን ወደፊት የሚያራምዱ ሀሳቦች እየተንጸባረቁ ይገኛሉ ሲሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አማካሪ ኮሚቴ አባል መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) ገለጹ። ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ይገኛል። በዚህም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። መብራቱ አለሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በምክክሩ ላይ ኢትዮጵያን ወደፊት ሊያራምዱ እና የታሪክ ቁስሎቻችንን ሊፈቱ የሚችሉ ሀሳቦች እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ምክክሩ አካታችነቱን የጠበቀ መሆኑን ገልጸው፤ተመካካሪዎችም ሀሳባቸውን በነጻነት እያቀረቡ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ ተደርጎ የማያውቅ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ተናግረዋል። ምክክሩ የተሻለች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ትልቅ ዕድል መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም የሚያስማሙን ጉዳዮችን የጋራ እያደረግን መቀጠል ይገባናል ብለዋል። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በሀገራቸው ጉዳይ እየመከሩ ነው፤ ይህም በፖለቲካ ምህዳሩ ምክክርን ባህል እያደረግን መምጣታችንን የሚያሳይ ነው ብለዋል። በዚህም የእኔ ሀሳብ ሁሌ ትክክል ነው የሚለውን እሳቤ በመተው በመመካከርና በመግባባት ሀገርን የሚያሻግሩ ሀሳቦችን እያንጸባረቅን ነው ብለዋል። በመሆኑም የምክክር ጉባኤው ለግጭት መንስኤ የሆኑ፣ዘላቂ ሰላምን፣ልማትን የሚያደናቅፉ ችግሮችን በመፍታት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል።
ማህበራዊ
የልብ በሽታን መከላከል የሚያስችል የሕክምና አቅምን የመገንባት ሥራ ላይ ትኩረት ተደርጓል
Aug 1, 2026 12
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት የልብ በሽታን መከላከል የሚያስችል የሕክምና አቅምን ለመገንባት እየሠራ እንደሚገኝ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ባለሙያዎች ማኅበር (ESCP) እና የፓን-አፍሪካ የልብ ሕክምና ማኅበር (PASCAR) በጋራ ያዘጋጁት "የESCP–PASCAR ኮንግረስ 2026" ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል፡፡ ጉባኤው በአፍሪካ የልብና የደም ሥር ጤናን ለማጠናከር፣ ሳይንሳዊ እውቀትን ለመለዋወጥና የባለሙያዎችን ትብብር ለማጎልበት ያለመ ነው። በመድረኩ ጤና ሚኒስቴርን ወክለው የተገኙት ፕሮፌሰር ስለሺ ጋሮማ፤ የልብና ደም ሥር በሽታዎች ለሰው ልጅ ሞት ምክንያት ከሆኑ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች መካከል ዋናው ነው ብለዋል። ሕመሙን በቅድመ-ምርመራ እና በጊዜው በሚገኝ ጥራት ያለው ሕክምና መከላከል የሚቻል ቢሆንም፣ አሁንም ሰፊ የቤት ሥራ በመኖሩ ምክንያት አምራች የሰው ኃይልን እያሳጣ ይገኛል ነው ያሉት። የበሽታውን ተጽዕኖ ለመቀነስ ቅድመ-ምርመራን፣ ድንገተኛና ልዩ ሕክምናዎችን፣ ማገገሚያዎችን እንዲሁም ምርምርና ፈጠራን ያካተተ ጠንካራ የጤና ሥርዓት መገንባት እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ጉባኤው የአፍሪካውያንን የተቀናጀ ሥራ ለማጠናከር ከፍተኛ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት በዚሁ ዘርፍ ላይ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ጠቁመው በመሠረታዊ የጤና እንክብካቤ ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማስፋፋት፣ ልዩ የልብ ሕክምና ባለሙያዎች ሥልጠናን በመጨመር፣ በከፍተኛ ሕክምና ማዕከላት ማስፋፊያ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በሽታዎችን በመከላከል፣ አስፈላጊ መድኃኒቶችንና ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ በኩል ከሙያ ማኅበራት፣ ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከልማት አጋሮችና ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በትብብር እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የልብ ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት ዶክተር ናትናኤል ታዬ፤ የሕክምና መገልገያዎች እጥረት፣ የአገልግሎት አለመዳረስ እና የወረፋ ጥበቃ በዘርፉ ዋና ዋና ፈተናዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ሆኖም እነዚህን ፈተናዎች በመቋቋም ልዩ የሕክምና አገልግሎቶችን ማስፋፋት፣ የሀገር ውስጥ ሥልጠናና ምርምርን ማጠናከር፣ ዲጂታል የጤና ቴክኖሎጂዎችን መተግበርና ዘርፉን የሚቀይሩ አጋርነቶችን የመገንባት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል። የፓን-አፍሪካ የልብ ሕክምና ማኅበር ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ሀቢብ ጋምራ፤ በሽታውን ለመከላከል የሙያተኞች የእውቀትና ልምድ ልውውጥ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፣ ጉባኤው የጋራ መፍትሔዎችን ለማስቀመጥ ይረዳል ብለዋል።
በሀረሪ ክልል የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ትኩረት ተሰጥቷል
Aug 1, 2026 92
አዲስ አበባ፤ ሀምሌ 25/2018(ኢዜአ):- በ2019 በጀት ዓመት የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ችግርን ለመቅረፍ እንደሚሰራ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር መዕረግ የሀረሪ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ ገለፁ። ቢሮው በተያዘው የ2019 በጀት ዓመት የአገልግሎት አሰጣጡን በማጎልበት ለነዋሪዎች ምቹ ከተማን ለመፍጠር እንደሚሰራም አስታውቀዋል። አቶ ሙክታር ሳሊህ እንደገለፁት ቢሮው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለሚያረጋግጡ ተግባራት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል። በክልሉ ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውል 20 ሄክታር መሬት በማዘጋጀት በተለያዩ አማራጮች ህብረተሰቡን የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለማድረግ እንደሚሰራም ገልፀዋል። እቅዱን በፍጥነት ተግባራዊ ለማድረግም ርብርብ ይደረጋል ብለዋል። በሌላ በኩል የከተማ፣ ገጠርና ሰፈር ፕላን ሽፋን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራና የካዳስተር ሽፋንን ለማሳደግ እንደሚሰራ ገልፀዋል። በተለይ የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በክልሉ የኮሪደር ልማትና የሌሎች ፕሮጀክቶች ግንባታን በተያዘላቸው ግዜ እንዲጠናቀቁም ይሰራል ብለዋል። በተለይ የተቋሙን የአገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ በማዘመን ለዜጎች ፍትሀዊ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚሰራ አቶ ሙክታር ሳሊህ ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ ህዝቦች መካከል ያለው ታሪካዊና ማህበራዊ መጋመድ የጠበቀ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jul 31, 2026 286
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ህዝቦች መካከል ያለው ታሪካዊና ማህበራዊ መጋመድ የጠበቀ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገሪቱ ወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የታሪክ አጋጣሚዎችን በመዳሰስ የህዝቦችን የቆየ ትስስር አብራርተዋል። ለ350 ዓመታት ገደማ የቆየውን የሸዋ ሱልጣኔት በምሳሌነት ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በወቅቱ ኦሮሞዎች፣ አማራዎች፣ አርጎባዎች፣ ጉራጌዎችና ሌሎች ብሔሮች በጋራ ይኖሩበት እንደነበር ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት በህዝቦቹ መካከል የጠበቀ መጋመድ መፈጠሩን ጠቁመው በኦሮሞና በአማራ ህዝቦች ዘንድ የቆየው የጉዲፈቻ ባህል ከማህበራዊ መስተጋብሩ ማሳያዎች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህም እስከ ነገስታት ደረጃ የደረሰ የባህል መጋራት፣ አብሮ የማደግና የማህበራዊ መስተጋብር ልምምድ እንዲጎለብት ማድረጉን አስረድተዋል። በታሪክ ሂደት በፖለቲካው መድረክ ስልጣንን ለማጠናከር ሲባል ይፈጸሙ የነበሩ ሰፋፊ ፖለቲካዊ ጋብቻዎች በህዝቦቹ መካከል እንደነበሩም ነው ያወሱት። በሌላ በኩል፣ በዜጎች የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴና ዝውውር የተፈጠረው ሰፊ የጋብቻና የዝምድና ትስስር ህዝቦቹ ከተጋመዱባቸው መንገዶች መካከል ተጠቃሽ ነው ብለዋል። በአጠቃላይ የአማራና የኦሮሞ ህዝቦች በቁጥራቸው መጠንና በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጣቸው ምክንያት በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ የነበራቸው መስተጋብር የጎላ እንደነበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝቦች በጋራ የመኖርና የመጋመድ ታሪክ እንዳላቸውም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስረዱት።
የአማራ ክልል ህዝብ እንደ ሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ሁሉ ለሀገር መጽናት እና ለፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል
Jul 31, 2026 277
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገር ጸንቶ መቀጠል እና ለፖለቲካ አውዱ መስፋት የአማራ ክልል ህዝብ ልክ እንደ ሌሎቹ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሁሉ ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ቆይታ አድርገዋል። የአማራ ክልል ህዝብ እንደ ማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ አሁን ባለውም ሆነ ከዚህ ቀደም በነበሩ ሀገራዊ ለውጦች ውስጥ የፖለቲካ ስሪቱ እንዲሻሻል፣ የኢኮኖሚ ጉዞው እንዲፋጠንና አካታች እንዲሆን ትግል ማድረጉንም አውስተዋል። ከለውጡ ማግስት በነበረው ጉዞ የአማራ ክልል ህዝብ እና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሁለት እጆቹን ዘርግቶ ለውጡን የተቀበለበትና ሀገር እንዲጸና የበኩሉን ድርሻ የተወጣበት እንደነበር ጠቁመዋል። ከለውጡ በፊት የነበረውን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መዘጋት ለመቀየር መንግስት የምህዳር ማስፋት ስራዎች ማከናወኑን ጠቁመው፤ በዚህ የመክፈት ሂደት ውስጥ መልካም ነገሮች መታየታቸውን ተናግረዋል። ይሁንና በተከፈተው መንገድ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለመገዳደርና ለመጉዳት የተሰለፉ ሃይሎች እንደነበሩም አንስተዋል። ምንም እንኳን ፈተናዎች ቢኖሩም የአማራ ክልል ህዝብ የመደመር መንገድ ብቸኛ አማራጭ መሆኑንና ለመበልጸግ የሚደረግ ጥረት ተገቢ መሆኑን ያመነ በመሆኑ፣ በዘንድሮው ምርጫ ያንን እምነቱን በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል። እንደ ሀገር ተከባብረን፣ ጥረንና ግረን አንዲት ታሪካዊት ሀገር ማጽናት የምንችል መሆኑን ህዝቡ ያመነበት ጊዜ እንደሆነም አስረድተዋል።
ኢኮኖሚ
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የአምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትና የቡና ወጪ ንግድን አሳድጓል
Aug 1, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የአምራች ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነትና የቡና ምርታማነትና ወጪ ንግድን በከፍተኛ በሁኔታ ማሳደጉን አምራቾችና ላኪዎች ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በሰጡት ማብራሪያ ሀገራዊ የሪፎርም ስራ ለውጭ ምንዛሬ ግኝት ስኬቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን መግለፃቸው ይታወሳል። ይህም በዘንድሮው ዓመት ከቡና ኤክስፖርት ብቻ 3 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ማስገኘት መቻሉን መግለፃቸውም እንዲሁ። የኦሮሚያ የቡና አቅራቢዎች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት እና የከብሬ ለኬ ቡና ላኪ ድርጅት ባለቤት ፈጠነ የኋላእሸት ለኢዜአ እንደገለጹት ከዚህ ቀደም በዘርፉ የነበሩ የፖሊሲ ክፍተቶች በቡና ምርትና ምርታማነት ላይ ተጽዕኖ ፈጥረው ቆይተዋል። ተግባራዊ የተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለዘርፉ ተዋናዮች መልካም እድል መፍጠሩን ጠቁመው ይህን ተከትሎም የቡና ኤክስፖርት በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍ እያለ መምጣቱን ገልጸዋል። የተደረገው ማሻሻያ በእሴት ሰንሰለቱ ላይ ያሉ ችግሮችን መለየት ማስቻሉን ይህም ቡና በቀላሉ ወደ ውጭ እንዲላክ ማድረጉን አስታውቀዋል። በተጨማሪም አሰራሮች ዲጂታላይዝ መደረጋቸው ዘርፉን ዘመናዊ እንዳደረገውና ለቡና ወጪ ንግድ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። ሪፎርሙን ተከትሎ በተሰሩ ስራዎች የቡና ምርታማነትና ጥራት በመጨመሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ መቻሉንም ገልጸዋል፡፡ በተለይም ባለፉት ሶስት ዓመታት የቡና ወጪ ንግድ በየዓመቱ በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍተኛ እድገት ማሳየቱን አብራርተዋል። በቀጣይም መንግስትና የዘርፉ ተዋናዮች ትብብራቸውን አጠናክረው ከቀጠሉ የወጪ ንግድ አፈፃፀምንና የዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነትን በዘላቂነት ማረጋገጥ እንደሚቻል አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ማሽነሪና መለዋወጫ አምራቾች ማህበር ፀሀፊ እና የፅዮን ኢንደስትሪያል ኢንጂነሪንግና ብረታ ብረት ኢንተርፕራይዝ ባለቤት ዮሃንስ ግርማ በበኩላቸው መንግስት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። በተለይም ተኪ ምርቶችን ለሚያመርቱና የወጪ ንግድ ኤክስፖርት ምርትን ለማሳደግ ለሚሰሩ አምራቾች ውጤታማ የሚያደርጉ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል። ለአምራች ዘርፉ በተሰጠው ትኩረትና እየተደረገ ባለው አጠቃላይ ድጋፍ የምርት ጥራትና ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ማጎልበት መቻሉንም ጨምረው አስታውቀዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እንደገለጹት፤ የኢንዱስትሪዎችን ችግር ከመለየት ጀምሮ በዘላቂነት ተወዳዳሪ ሊሆኑ የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቷል። የአምራች ኢንዱስትሪ ችግሮችን ለመፍታት የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በዘርፉ ከፍተኛ ውጤቶች መመዝገባቸውንም አመላክተዋል። ይህም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የፋይናንስ ማነቆ በመፍታት ቀደም ሲል 40 ቢሊየን ብር የነበረውን የብድር መጠን ወደ 115 ቢሊየን ብር ከፍ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በዚህም የኢንዱስትሪዎቻችን ተወዳዳሪነት፣ ምርታማነት፣ ትርፋማነትና የመስፋፋት ዕድል ከፍ እያለ መምጣቱን ገልጸዋል።
በባሌ ዞን ከበልግ እርሻ እስካሁን 6 ነጥብ 9 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተሰብስቧል
Aug 1, 2026 155
ሮቤ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን በበልግ ወቅት ከለማወ መሬት ከ6 ነጥብ 9 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። በዞኑ በሜካናይዜሽን የታገዘው የሰብል ስብሰባ ሒደት በድህረ ምርት ወቅት ሊያጋጥም የሚችለውን የምርት ብክነት ለመቀነስ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለውም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አልይ መሐመድ እንዳሉት፤ በዞኑ በበልግ ወቅት ከለማው 277 ሺህ 182 ሄክታር መሬት ውሰጥ እስካሁን በተደረገ ጥረት ስድስት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል ምርት ተሰብስቧል። ይህም በሰብል ከተሸፈነው አጠቃላይ መሬት 90 በመቶውን እንደሚሸፍን ተናግረዋል። የምርት አሰባሰብ ሂደቱ ተጠናክሮ መቀጠሉንና በአጠቃላይ በምርት ዘመኑ ከለማው መሬት ስምንት ነጥብ ሦስት ሚሊየን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። በበልግ ወቅት ከለማው መሬት 107 ሺህ ሄክታሩ በስንዴ ሰብል መልማቱን ጠቁመው እስከ አሁን ከተሰበሰበው 82 ሺህ ሄክታር መሬት 3 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል የስንዴ ምርት መሰብሰቡን አስታውቀዋል። የደረሱ ሰብሎችን ወቅቱን ካልጠበቀ ዝናብ ለመታደግ በኮምባይነር እየተደረገ ካለው የመሰብሰብ ስራ በተጓዳኝ በጥቃቅን ማሽነሪዎችና በሰው ጉልበትም እየተሰበሰበ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም በመካናይዜሽን ሰብልን ለመሰብሰብ የሚደረገው ጥረት ሊደርስ የሚችለውን የምርት ብክነት ከማስቀረቱም በላይ ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለገበያ ለማቅረብ የጎላ አስተዋፅኦ እንዳለውም አክለዋል። በዞኑ በበልጉ ወቀት በተለያዩ የሰብል አይነቶች ከተከሸፈነው ማሳ 73 በመቶ የሚሆነው የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችና ሙሉ ፓኬጆችን በመጠቀም በኩታ ገጠም የለማ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አብዱልሀኪም አልይ ናቸው። በዞኑ በመኸር፣ በበልግና በመስኖ አማራጮች ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማና፣ ከ20 ሚሊየን ኩንታል በላይ ዓመታዊ ምርት እንደሚጠበቅ አመልክተዋል። ከሲናና ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል ሐጅ ሳፊ አህመድ በሰጡት አስተያየት፤ ሰብልን በኮምባይነር በመሰብሰብ ይደርስ የነበረውን ብክነት ማስቀረት መቻላቸውን ተናግረዋል። ከአካባቢያቸው አርሶ አደሮች ጋር በመቀናጀትም በኩታገጠም አሰራር በመታገዝ መሬታቸውን ማልማታቸው ምርታማነታቸውን እንዳሳደገላቸው አመልክተዋል። በኦሮሚያ ክልል በዝናብ ውኃ አማራጭ በመኽርና በልግ አዝመራ በዓመት ሁለቴ ከሚመረትባቸው አካባቢዎች አንዱ ባሌ ዞን ነው። በዞኑ ከሚያዝያ ወር መጨረሻ እስከ ነሐሴ መገባደጃ ያለው ጊዜ የበልግ የምርት ወቅት መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ንግድ ትስስርና ዕድገት ቁልፍ ሀገር ነች
Aug 1, 2026 86
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናዊ እና አህጉራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሁም በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ወሳኝ ሚና እየተጫወተች የምትገኝ ቁልፍ ሀገር መሆኗን በአፍሪካ የንግድና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራው 'ትሬድ ካታሊስት አፍሪካ' ገለጸ። ኢትዮጵያ ያሏት የታሪክ፣ የስነ-ህዝብ፣ የመሰረተ ልማት እና የጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ፀጋዎች በቀጣናው ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማፋጠን ወሳኝ ድርሻ እንድትጫወት አስችለዋታል፡፡ እንዲሁም የሃይል እና ትራንስፖርት መረቦችን ለመዘርጋትና በአህጉር ደረጃ የፖሊሲ እና የዲፕሎማሲ አቅጣጫዎችን ለመቀየስ የሚያስችላትን የጎላ ድርሻ ይሰጣታል። የ'ትሬድ ካታሊስት አፍሪካ' ዋና ሥራ አስፈጻሚ አደሬ አዳንኮ ኒያንጎ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ ሰፊ የሕዝብ ቁጥር፣ ትልቅ ኢኮኖሚና በርካታ አምራች ወጣቶች ያላት ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። ይህ መልካም አጋጣሚ ሀገሪቱ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንድታበረክትና ተጽዕኖዋን እንድታሰፋ የሚያስችላት መሆኑንም አስታውቀዋል። በሀገሪቱ ውስጥ በርካታ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ዘርፎች ለልማትና ለስኬት ሰፊ እድል ይዘው እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ በተለይም በግብርና እና በግብርና ማቀነባበር መስኮች ላይ ያሉ ሰፊ ዕድሎችን አንስተዋል፡፡ እንዲሁም እንደ ጤና፣ ትምህርት እና የፋይናንስ አገልግሎቶች ባሉ ቁልፍ ዘርፎችም ትልቅ የእድገት አቅም መኖሩን ጨምረው አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትኩረት እየተሰጣቸው ያሉት ወሳኝ ማዕድናት የኢትዮጵያን ሀገራዊ ብልጽግና በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም እንደሚያስችሉ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በቀጣናዊ እና አህጉራዊ የኢኮኖሚ እድገት እንዲሁም በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ወሳኝ ሚና እየተጫወተች የምትገኝ ቁልፍ ሀገር ናት ብለዋል። በዩናይትድ ኪንግደም በሚገኘው ዓለም አቀፍ ገለልተኛ የፖሊሲ እና ጥናት ተቋም (ODI) ዋና ተመራማሪ ማክሲምን ዲባራ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉር በፍጥነት እያደጉ ካሉ የኢኮኖሚ ማዕከላት አንዷ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የኢኮኖሚ እድገት እያሰመዘገበች እንደምትገኝ አንስተው፤ በተለይም በግብርና እና በአምራች ዘርፎች የሚታየው የእድገት እንቅስቃሴ ከፍተኛ መሆኑን አስታውቀዋል ይህ እድገት ኢትዮጵያ የባህረ ሰላጤው ሀገራት ከቀሪው የአፍሪካ አህጉር ጋር የሚኖራቸውን የኢኮኖሚ ትስስር የሚያሳልጥ ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን እንደሚያስችላት ገልጸዋል። እየተከናወኑ ያሉ የኢንዱስትሪና የግብርና ልማት ሥራዎችም ለሀገራቱ የምግብ ዋስትና እና የኢንቨስትመንት ፍላጎቶች ተስማሚ ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ተመራማሪው ይህም ኢትዮጵያን አጠቃላይ አህጉራዊውን የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የሚያስተስስር ቁልፍ ማዕከል እንደሚያደርጋት አስታውቀዋል።
በጅማ ዞን በመኸር እርሻው 930 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር ተሸፍኖ እየለማ ነው
Aug 1, 2026 131
ጅማ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን በመኸር እርሻው 930 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር ተሸፍኖ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ በ2018/19 ምርት ዘመን መኸር ወቅት ለሰብል ምርትና ምርታማነት እድገት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በመኸር እርሻው 883 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር በመሸፈን 36 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል። እስካሁን በተደረገ ጥረት ከእቅድ በላይ 930 ሺህ ሄክታር መሬት ታርሶ በበቆሎ፣ በጤፍ፣ በሩዝ እና በሌሎች ሰብሎች ዘር ኘሸፈኑን ገልጸዋል። በዘር ከተሸፈነው ውስጥ 200ሺህ ሄክታሩ በበቆሎ ዘር መሸፈኑን ጠቁመው ቀድሞ የተዘራ በመሆኑም አሁን ላይ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ተናግርዋል። በምርት ወቅቱ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተሰጠው ትኩረት አብዛኛው ሰብል በኩታ ገጠም የተዘራ መሆኑን አመልክተዋል። በዞኑ ከሚገኙ የግብርና ግብዓት ማዕከላትና ዩኒየኖች ጋር በመቀናጀትም የግብርና ግብዓቶችን በተሳካ መልኩ ማሰራጨት መቻሉንና ለአርሶ አደሩ እየተደረገ ያለው የክትትልና ሙያዊ ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል። በዞኑ ሊሙ ኮሳ ወረዳ በግብርና ልማት ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል ሚልኮ ሙዲን ዓምና በቆሎን ከሌሎች የአካባቢው ወጣቶችና አርሶ አደሮች ጋር በክላስተር በማልማት የተሻለ ምርት ማግኘቱን አስታውሷል። በዘንድሮ ምርት ዘመንም ቀደም ብሎ የመሬት ዝግጅት በማድረግና አስፈላጊውን የግብርና ግብዓት በመጠቀም የዘራውን በቆሎ እየተንከባከበ መሆኑን ተናግሯል። ሌላው የወረዳው አርሶ አደር ጌታቸው አሊ በበኩላቸው ዘንድሮ በቆሎን በስፋት መዝራታቸውንና የበቆሎ ምርጥ ዘር በወቅቱ በማግኘታቸው የዘር ስራውን በወቅቱ ለማከናወን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው አስረድተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የተጀመረው የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ በቴክኖሎጂ፣ በፍጥነት፣ በፈጠራ፣ በጥራትና በታማኝነት ማስፋፋቱ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jul 30, 2026 503
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦ የተጀመረው የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ በቴክኖሎጂ፣ በፍጥነት፣ በፈጠራ፣ በጥራትና በታማኝነት ማስፋፋቱ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገነዘቡ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ሀገር በቀል ሆኖ በሰባት አምዶች ተደራጅቶ የተቀረጸውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር አፈጻጸም ሪፖርት ለሪፎርም ምክር ቤቱ ቀርቦ በዝርዝር ተገምግሟል ብለዋል። አምዶቹም ዘመኑን የዋጀና በተዋረድ የተናበበ አደረጃጀት፣ ብቃት ያለው የሰው ኃይል ስምሪት፣ ብዝሃነት፣ ዲጂታላይዜሽ፣ የለውጥ አመራር እና የአገልግሎት ማሻሻያን የያዘ መሆኑን ገልጸዋል። አፈጻጸሙም ፍጥነትን፣ ፈጠራን፣ ፈጻሚዎቹን ባለቤት ማድረግንና ዘላቂ ሥርዓት ግንባታን መሠረት ተደርጎ በጥብቅ ዲስፕሊንና በእውቀት ውጤታማ እና ተስፋ በሚሰጥ ሁኔታ እየተፈጸመ መሆኑንም አይተናል ነው ያሉት በመልዕክታቸው። በሪፖርቱ ሰው ተኮር በሆነ ሁኔታ የመሶብ አገልግሎትን በማስፋፋት ሂደት ጉልህ የሚባል መሻሻል በየከተሞቹ ታይቷል ሲሉም አስታውቀዋል። በመልዕክታቸው አክለውም በአገልግሎት ማሻሻያ ረገድ ትልቅ ለውጥ ማምጣት የምንችል መሆኑንና በዜጎች በኩል የነበረውን እሮሮ መፍታት መጀመራችን በተግባር የታየበትም ጉዳይ ነው ብለዋል። የተጀመረው የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ በቴክኖሎጂ፣ በፍጥነት፣ በፈጠራ፣ በጥራትና በታማኝነት ማስፋፋቱ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋለ። ለዚህም ሥራ የጠራ መረጃ ማደራጀት፣ ቴክኖሎጂን ማበልጸግና የሰራተኞችን ብቃት ማጠናከር የቀጣይ ትኩረት እንዲሆን በምክር ቤቱ አቅጣጫ መቀመጡንም ገልጸዋል።
የዲጂታል መታወቂያ የምዝገባ ሂደት እና ‘የ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደርስ’ ኢኒሼቲቭ ትግበራ ተጠናክሮ ይቀጥላል-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jul 30, 2026 391
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የዲጂታል መታወቂያ የምዝገባ ሂደት እና ‘የ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደርስ’ ኢኒሼቲቭ ትግበራ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የብሔራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ዛሬ ስብሰባውን ማድረጉን ገልጸዋል። ምክር ቤቱ በአመቱ ውስጥ እንዲፈፀሙ ያስቀመጣቸውን ተግባራት አፈፃፀም በጥልቀት በማየት አቅጣጫ ማስቀመጡን አመልክተዋል። የብሔራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤቱ አጠቃላይ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የስራ ክንውን፣ የዲጂታል መታወቂያ የምዝገባ ሂደት እንዲሁም ‘የ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደርስ’ ኢኒሼቲቭ ትግበራ አፈጻጸምን ገምግሞ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል። ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያ በመከናወን ላይ የሚገኙ አዳዲስ የዲጂታል ስራዎች ከዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ጋር ያላቸውን ተጣጣሚነትን በውይይታችን ተመልክተናል ሲሉ ተናግረዋል። የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታችን በእመርታ የሚያድግበት ዘመን ላይ እንደመሆኑ፤ ምክር ቤቱም ለዚሁ ዕድገት ተገቢውን ሚና ለመወጣት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር የተገልጋይን እንግልት ለመቀነስ አስችሏል
Jul 30, 2026 204
ወራቤ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ) ፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመንግስት አገልግሎትን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር የተገልጋይን እንግልት ለመቀነስ ማስቻሉን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ ገለፁ። የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የሚመክር መድረክ በወራቤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በዚህ ወቅት አቶ አንተነህ እንዳሉት፤ በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመንግስት አገልግሎትን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር የተገልጋይን እንግልት ለመቀነስ አስችሏል። ለዚህም በተቋማት ግንባታና በሰው ኃይል ማብቃት ላይ በመሥራት ሰባት የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል። በዚህም በመንግሥት የሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሠራሮችን ከመቅረፍ በተጨማሪ የማኅበረሰቡን እርካታ እያሳደገ መምጣቱን ገልጸዋል። የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ በበኩላቸው፤ በክልሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራን ለማሳካት በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የሰው ኃይል ልማት ላይ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ከ235 ሺህ በላይ ዜጎች ስልጠናውን መውሰዳቸውንና ከእነዚህም ውስጥ ከ185 ሺህ በላይ የሚሆኑት የእውቅና ሰርተፊኬት ማግኘታቸውን አስረድተዋል። ስልጠናውን ወስደው እውቅና ያገኙትንም የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። በዞኑ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራ ዘርፈ-ብዙ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙበራ ከማል ናቸው። በዞኑ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን የማስፋፋቱ ስራ የመንግሥት አገልግሎትን ለማዘመንና ለወጣቶች የሥራ ዕድልን ለመፍጠር እየዋለ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ይህም የተገልጋዩን ማኅበረሰብ ጊዜ፣ ጉልበትና እንግልት በማስቀረት ረገድ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበበት እንደሚገኝ ገልጸዋል። በወራቤ ከተማ ተግባራዊ የተደረገውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ወደ ሌሎች የዞኑ መዋቅሮች የማስፋፋት ሥራ ስለመጀመሩም አክለው ገልጸዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ቀልጣፋ የመንግስት አሰራር እንዲሰፍን እያደረገ ነው
Jul 29, 2026 297
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ) :-መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ቀልጣፋ የመንግስት አሰራር እንዲሰፍን እያደረገ ነው ሲሉ ምሁራን ገለጹ። በፌዴራል ደረጃ በአዲስ አበባ የተጀመረው የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በማስፋት ዘመናዊ አገልግሎት እየተፈጠረ ነው። በዚህም አገልግሎቱ በተጀመረ አንድ ዓመት ባልበለጠ ጊዜ 102 ማዕከላት፣ ሦስት ተንቀሳቃሽና አንድ የተቀናጀ መተግበሪያ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ አማራጮችም 953 ተቋማትን በማስገባት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ዜጎች አገልግሎት አግኝተዋል፡፡ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥትን አገልግሎት ጥራት በማሻሻል የተገልጋዮችን እርካታ በማሳደግ የመልካም አስተዳደር ሥርዓትን እያሰፈነም ይገኛል፡፡ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዘርፉ ምሁራን ፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት በሀገር ደረጃ ትልቅ የለውጥ እርምጃ እንዲሁም የመልካም አስተዳደርና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና አመራር ትምህርት ክፍል መምህር ኡጁሉ ኡኮክ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ህዝቡ ለአንድ አገልግሎት ወደተለያዩ መሥሪያ ቤቶች መመላለስ ሳይጠበቅበት ጊዜውንና ገንዘቡን በአግባቡ እንዲጠቀም የሚያስችል ትልቅ ማሻሻያ ነው። አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ከብልሹ አሠራር የጸዳ ሥርዓት በመፍጠር ግልጽነትና ተጠያቂነትን እንደሚያሰፍን ገልጸዋል። ይህ አሰራር ብልሹ አሰራርን በማስቀረት፣ ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥንና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የልማታዊ ተግባቦትና የሚዲያ ጥናት መምህርና ተመራማሪ ዘለቀ ተሾመ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቱ ህብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ላነሳቸው የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠ መሆኑን አንስተዋል። መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከዚህ ቀደም የነበረን መጉላላት በማስቀረት የተቀላጠፈ፣ ምቹና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለማግኘት ማስቻሉ ለዜጎች ትልቅ እፎይታን የፈጠረ ነው ብለዋል፡፡ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ማደራጀት የተገልጋዩን ጊዜና ወጪ በመቀነስ የመንግስትን የአሰራር ቅልጥፍናና ከህዝብ ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክር ትልቅ እርምጃ መሆኑን አስታውቀዋል። አሰራሩ በአፍሪካ ደረጃም በጥሩ አርዓያነት የሚጠቀስ መሆኑን አክለዋል፡፡
ስፖርት
ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በስፖርት መሰረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ መስራት ይገባል
Jul 26, 2026 398
ሀዋሳ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እግር ኳስ ተወዳዳሪና ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በስፖርት መሠረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ የሚሰሩ ስራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተጠቆመ። እ.አ.አ. በ1957 የተመሰረተው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መስራች ከነበሩ ሀገራት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እግር ኳስ ዕድገት ትልቅ አሻራ አሳርፋለች። የአፍሪካ እግር ኳስ በዓለም መድረክ የሚገባውን ቦታ እንዲይዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉት የካፍ ፕሬዝዳንት የነበሩት የይድነቃቸው ተሰማ ሀገር ኢትዮጵያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የእግር ኳስ አፍቃሪያን ያሉባትም ናት። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እግር ኳስ ዕድገት ያኖረችውን አሻራና የቀደመ ገናና ታሪክ በማንሳት የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ጥያቄ ማቅረቧም ይታወቃል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ዋና አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ እና የክለቡ ተጫዋች ሁሴን ጠሃ፤ በኢትዮጵያ ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት በመሰረተ ልማትና ታዳጊዎች ላይ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ በእግር ኳሱ የላቀ ችሎታ ያላቸው ተጫዋቾች እንዳሏት አንስተው ተወዳዳሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት ዕድሎችን ለመጠቀም ብዙ ልንሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። የ2018ቱ የሲቢኢ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው ቡድን አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ እንደገለጸው፤ ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት ሌላው ዓለም የሚሰራውን መስራት መቻል አለብን ። የስፖርት መሰረተ ልማትና የታዳጊ ስልጠና ማዕከላትን ማጠናከር፤ የምልመላ ስርዓትና የውድድር ዕድሎችን ማስፋት ቀዳሚዎች መሆናቸውን አንስቷል። ዕምቅ ችሎታ ያላቸው ተጫዋቾች የሚፈሩባቸው ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የሚደረጉ ስልጠናዎችና ውድድሮች ላይ ማተኮር እንደሚገባም አክሏል። አሰልጣኞችን ልምድ ባላቸው ሀገራት ማስተማር፣ ወጥ የሆነ የስልጠና ማኑዋል ማዘጋጀትና ሳይንሳዊ የሆነ የምልመላ ስርዓት መዘርጋት ሌላው ሊተኮርበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አንስቷል። መንግስት የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ጥያቄ ማቅረቡ በስፖርቱ ዘርፍ ከፍተኛ የሆነ መነሳሳትን እንደሚፈጥር የጠቀሰው አሰልጣኝ ያሬድ ዕድሉን መጠቀም ይገባናል ሲል ገልጿል። ለዋናው ብሔራዊ ቡድን የመጫወት ህልም ይዞ እየሰራ ያለው የክለቡ ከ20 ዓመት በታች የግራ መስመር አጥቂ ሁሴን ጠሃ በበኩሉ፤ ተፎካካሪ ብሔራዊ ቡድን ለመፍጠር ታዳጊዎችና የስልጠና ሜዳዎች ሊጠናከሩ ይገባል ነው ያለው።
የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
Jul 24, 2026 467
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን የርገን ክሎፕን የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የ59 ዓመቱ ጀርመናዊ የአራት ዓመት ውል የተፈራረሙ ሲሆን ስምምነቱ አሰልጣኙን እስከ 2030 የዓለም ዋንጫ መጨረሻ ድረስ የሚያቆያቸው ነው። ክሎፕ በቦታው የተኩት በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ጀርመን በ32ቱ ዙር በፓራጓይ ተሸንፋ ከውድድሩ ውጪ ከሆነች በኋላ ከኃላፊነታቸው የለቀቁትን ጁሊያን ናጌልስማንን በመተካት ነው። ከሊቨርፑል የዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ የሬድ ቡል ሳልስበርግ የዓለም እግር ኳስ ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት ክሎፕ፣ የጀርመን እግር ኳስን እንደገና ወደ ቀደመ ገናናነቱ የመመለስ ትልቅ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ክሎፕ ከጀርመን ብሔራዊ ቡድን ጋር የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም. በዩኤፋ ኔሽንስ ሊግ (Uefa Nations League) ከኔዘርላንድስ ጋር ያደርጋሉ።
የዓለም አትሌቲክስ የአትሌት ትዕግስት አሰፋ የሴቶች ብቻ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን አፀደቀ
Jul 23, 2026 476
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም አትሌቲክስ የኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ የሴቶች ብቻ (women’s only) የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን ዛሬ ማፅደቁን ይፋ አድርጓል። አትሌት ትዕግስት እ.አ.አ አፕሪል 26 / 2026 በለንደን ማራቶን 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ከ41 ሴኮንድ በመግባት እ.አ.አ በ2025 በራሷ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን በዘጠኝ ሴኮንድ በማሻሻል አሸንፋለች። የዓለም አትሌቲክስ የአትሌቷን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረ ወሰን ዛሬ ማፅደቁን አስታውቋል። የሴቶች ብቻ (women’s only) የዓለም ክብረ ወሰን ሴቶች ብቻ በሮጡበት ውድድር ብቻ የተመዘገበ የዓለም ፈጣን ሰዓት ማለት ነው። የዚህ የዓለም ክብረ ወሰን አመዘጋገብ በሴቶች ውድድር ላይ የወንድ አሯሯጮች ወይም ወንዶች ተቀላቅለው ሲሮጡ (አጠቃላይ ሩጫ) ከሚመዘገበው የዓለም ክብረ ወሰን ጋር የሚለያይ ነው። ወንዶች በሴቶች ውድድር ላይ መኖራቸው የውድድሩን አዝማሚያ እና ሴቶች የሚያስመዘግቡት ሰዓት ላይ ተጽእኖ እንደሚያሳድር የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል። ሴት እና ወንድ ተደባልቀው በሚሮጡበት አጠቃላይ የሴቶች ማራቶን ውድድር የዓለም ክብረ ወሰንን (Overall women's world record) የያዘችው ኬንያዊቷ አትሌት ሩት ቼፕጌቲች ናት። ሩት እ.አ.አ በ2024 በቺካጎ ማራቶን 2 ሰዓት ከ9 ደቂቃ ከ56 ሴኮንድ በመግባት ክብረ ወሰኑን ጨብጣለች። የዓለም አትሌቲክስ ከአትሌት ትዕግስት በተጨማሪ ሰባት የዓለም ክብረ ወሰኖችን ማጽደቁን አስታውቋል። እውቅናና ፈቃድ በተሰጣቸው ውድድሮች ላይ ማሸነፍ፣ የውድድር ሜዳዎቹ የሚፈለገውን መስፈርት ያሟሉ መሆንና አትሌቶች በአበረታች ቅመም ምርምራ ውጤት ጤነኛ መሆናቸው መረጋገጥ አትሌቶች የዓለም ክብረ-ወሰን ባለቤት የሚሆኑባቸው ዋነኛ ቅደመ-ሁኔታዎች ናቸው።
አካባቢ ጥበቃ
የዛሬ ችግኞች የነገ የሀገር ትሩፋቶች
Aug 1, 2026 34
አረንጓዴ አሻራ በአፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ሀገር በቀል ምላሾች መካከል በዋናነት ይጠቀሳል። ኢኒሼቲቩ ሀገር በቀል እውቀት፣ የጋራ ተግባር እና መጠነ ሰፊ የማህበረሰብ ተሳትፎን በማቀናጀት ስኬታማ የሆነ ለዓለም የሚደርስና ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር የሚያሳይ ነው። አረንጓዴ አሻራ ከአካባቢ ጥበቃ ትሩፋቶቹ፣ የተራቆተ መሬትን ወደ ነበረበት ከመመለስ፣ የውሃ ሀብት አስተዳደርን በመጨመር እና የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ አንጻር ካለው ፋይዳ ባሻገር አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት ከውጭ መፍትሄ እስኪመጣ ከመጠበቅ በራሷ አቅም መፍትሄን ማመንጨት እንደምትችል የሚያሳይ ነው። የአረንጓዴ አሻራ ግብ ችግኝ መትከልና የአካባቢ ጥበቃ ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ግንባታ፣ የህዝብ አንድነት እና የኢኮኖሚ ልማት ማዕከል ማድረግ ሲሆን ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በቀጥታ ተሳታፊ እንዲሆኑና ለጋራ ብልጽግና በጋራ እንዲሰሩ እድል የፈጠረ ህዝባዊ ንቅናቄም ነው። ይህንኑ ሀገራዊ ኢኒሼቲቭ ይበልጥ ለማጠናከር “ተስፋን እንትከል!” በሚል መሪ ሀሳብ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አማካኝነት በይፋ ተጀምሯል። በዚህ ዓመት ብቻ ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን፤ ይህም ቀደም ሲል ተይዞ የነበረውን የ48 ቢሊዮን ችግኞች አጠቃላይ ግብ ወደ 65 ቢሊዮን ከፍ ያደረገ ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ነው። በተከታታይ በተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ስራም በ2010 ዓ.ም. 17 ነጥብ 2 በመቶ የነበረው የደን ሽፋን 2016 ዓ.ም. ላይ 23 ነጥብ 6 በመቶ ሊደርስ ችሏል። ለበርካታ አስርት ዓመታት የቆየውን የመሬት መራቆት መግታትም ተችሏል። በተጨማሪም ይህ ኢኒሼቲቭ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። የአረንጓዴ ዐሻራ ፋይዳ ግን የአፈርና ውኃ ጥበቃ እንዲሁም የደን ሽፋን መጨመር ብቻ አይደለም፤ የተፈጥሮ ደኖች መስፋፋታቸው ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የማር ምርትን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያድግና የስርዓተ-ምግብ መሻሻል እንዲረጋገጥ አድርጓል። አሁን ደግሞ የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ቀጠሮ ተይዟል። ይህ ታሪካዊ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላውን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት ውድ የሀገሬ ልጆች፤ በእነዚህ ቀናት አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ፣ በቁርጠኝነት እንድትነሱ እና በአንድነታችን የምናስመዘግበውን ድል እውን እንድናደርግ ጥሪዬን አቀርባለሁ። በጋራ ተስፋን እንትከል! ብለዋል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ፣ ዛፎችን የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ የተስፋ፣ የህብረት እና የሀገራዊ ህዳሴ ምልክት ነው። የዛሬዎቹ ችግኞች የነገዎቹ ደኖች፣ የነገዎቹ የውሃ ምንጮች እና የነገው ትውልድ ንጹህ አየር ናቸው። ይህ ንቅናቄ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት ያላትን ቁርጠኝነት ለዓለም ያሳየችበት፣ ዜጎቿም ለሀገራቸው እድገት በጋራ ሲቆሙ ምን ያህል ታላቅ ነገር መስራት እንደሚችሉ ያስመሰከሩበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። ዛሬ የተተከለው እያንዳንዱ ችግኝ ለነገዋ አረንጓዴ፣ ሰላማዊ እና የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚቀመጥ ጠንካራ የማዕዘን ድንጋይ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት የኢትዮጵያን የአየር ንብረት ዲፕሎማሲ በተግባር ያሳየ ነው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)
Aug 1, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት ሀገሪቱ የምትከተለውን የአየር ንብረት ዲፕሎማሲ በተግባር የሚያሳይ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቢሾፍቱ ከተማ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዷል። በመርሃ ግብሩ የጎረቤትና የሌሎች አፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች መሆኗን ማሳያ ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት እና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስተዋወቅን ጨምሮ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ሀገሪቱን በአየር ንብረት ዲፕሎማሲ ቀዳሚ ማድረጋቸውንም አብራርተዋል። ችግኝ ተከላው ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ያላትን ቁርጠኝነት በተጨባጭ ያሳየችበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ለቀጣናችንና ለአህጉራችን ለተሻለ የወደፊት ጊዜ፣ ለሰላምና ለአብሮነት ተስፋን እንተክላለን ሲሉም ተናግረዋል። ከሱዳን፣ ከኬንያ እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዲፕሎማቶች ጋር የተካሄደው የችግኝ ተከላ ልምድን ለማካፈል፣ ቀጣናዊ ትስስርንና ትብብርን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልጸዋል። የሚተከሉት ችግኞች ሲያድጉና ሲያፈሩ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዳላቸው የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር እንዲጸድቁና የሚፈለገውን ጥቅም እንዲሰጡ አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በወላይታ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል
Aug 1, 2026 67
ወላይታ ሶዶ ፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ከ6 ሺህ 450 ሄክታር በላይ መሬት ላይ እንደሚተከሉ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዘማች ሶርሳ (ዶ/ር) በዞኑ ለዘንድሮ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቂ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። በዞኑ በሚገኙ ሁሉም የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ለመርሃ ግብሩ በተለዩ የመትከያ ቦታዎች ኅብረተሰቡን በንቃት ለማሳተፍ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ እየተሠራ ይገኛል። በመርሃ ግብሩም የፍራፍሬ፣ የቀርከሃ፣ የውበትና ጥላ፣ የጥምር ደን እንዲሁም ሌሎች ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን በመትከል ከ6 ሺህ 450 ሄክታር በላይ መሬት ይሸፈናል ብለዋል። ለዚህም የጉድጓድ ቁፋሮን ጨምሮ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት በሙሉ መጠናቀቁን የጠቆሙት ኃላፊው፤ በዕለቱ ከ828 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ተናግረዋል። ለዘመቻው መሳካትም በሳይንሳዊ ዘዴ የመትከያ ቦታዎች ልየታ መደረጉን በመጠቆም ሁሉም የአካባቢው ነዋሪዎች በነቂስ ወጥተው አሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ አቅርበዋል። «የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ከተጀመረ ወዲህ ገላጣ የነበሩ መሬቶች ለምተውና የደረቁ ምንጮች በመፍለቃቸው አርሰንም ሆነ አርብተን የተሻለ ኑሮ መምራት ጀምረናል» ያሉት ደግሞ በዞኑ ዳሞት ጋሌ ወረዳ የሻኪሾ ሾኔ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ገላነህ ቱማቶ ናቸው። ከዚህም የተነሳ ክረምቱ ከገባ ጀምሮ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች መትከል መጀመራቸውን አንስተው ሰኞ ዕለት ለሚካሄደው የአንድ ጀምበር ተከላም መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በወረዳው የቡጌ ቀበሌ አርሶ አደር ነጋ ጌቶ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም የተከሏቸው የፍራፍሬ እና ሌሎች ችግኞች ደርሰው በመሸጥ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ያነሳሉ። ዘንድሮም ከ100 በላይ ችግኞችን ለመትከል በግብርና ባለሙያ ድጋፍና ትምህርት መሠረት የጉድጓድ ቁፋሮ ማከናወናቸውን ጠቁመዋል።
በሸገር ከተማ በአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በ875 ሄክታር መሬት ላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ይተከላሉ
Aug 1, 2026 68
ሸገር፤ ሐምሌ 25/2018 (ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ በአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በ875 ሄክታር መሬት ላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ የከተማዋ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። በፊታችን ሰኞ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም "ተስፋን እንትከል!" በሚል መሪ ሐሳብ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካል የሆነው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ በሀገር አቀፍ ደረጃ ይካሄዳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያውያን በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ ለመሥራት እንዘጋጅ በማለት ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል። "በእነዚህ ቀናት ውድ የሀገሬ ልጆች አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉና በጋራ ተስፋን እንትከል" በማለትም መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። መርሃ ግብሩን አስመልክተውም የከተማው ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች የደረቁ ምንጮችን በማጎልበትና የአፈር ለምነትን በመመለስ ምርትና ምርታማነትን አሳድገዋል። በዘንድሮው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በከተማው በ875 ሄክታር መሬት ላይ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ለሚተከሉ ችግኞች የቦታ ልየታ፣ የጉድጓድ ዝግጅት፣ እንዲሁም የማጓጓዝ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። የተዘጋጁ ችግኞችም ለምግብ፣ ለከተማ ውበት፣ ለደን ሽፋንና ለሌሎች ተያያዥ አገልግሎቶች የሚውሉ መሆናቸውን አንስተዋል። በዕለቱ ለተከላው 210 ሺህ የሚጠጋ የኅብረተሰብ ክፍል በንቃት እንደሚሳተፍም አክለዋል። ተግባሩ ለከተማዋ አረንጓዴ ልማት ጠንካራ መሠረት እንደሚጥል የገለጹት ኃላፊው፤ ስኬቱን የበለጠ ለማጠናከር ከተከላው ባሻገር የእንክብካቤና ጥበቃ ሥራዎች ላይ ትኩረት መደረጉንም አብራርተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 274
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 792
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ተጠናቀቀ
Jul 29, 2026 837
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ ከትናንት ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዘጋጅነት የተካሄደው የሁለት ቀናት ስብሰባ ላይ የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ተሳትፈዋል። ሚኒስትሮቹ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ቁልፍ አጀንዳዎችና የአፍሪካን አህጉራዊ ትስስር ማፋጠን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። በስብሰባው ሚኒስትሮቹ የአጀንዳ 2063 አፈፃፀም የሚከታተለውን ኮሚቴ ሪፖርት እንዲሁም የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እና በአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ወቅት ያሉ ስምምነቶችና የአሰራር ማዕቀፎች ያሉበትን የትግበራ ደረጃ ገምግመዋል። በተጨማሪም የ2026ቱን የህብረቱን የዓመቱ መሪ ሀሳብ የእስካአሁን የአፈጻጸም ሂደት ላይም መክረዋል። ስብሰባው እ.አ.አ. በ2017 በህብረቱ አባል ሀገራትና መንግስታት መሪዎች የፀደቀውን ተቋማዊ ማሻሻያ መነሻ ያደረገ ነው። ከስብሰባው የተገኙ ውጤቶች አህጉራዊ ዘላቂ ልማትን፣ ትስስርና ብልፅግናን እውን ለማድረግ የተቀረፀውን የአፍሪካ ህብረት የረጅም ጊዜ መሪ እቅድ (አጀንዳ 2063) ስኬታማ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
አፍሪካ ከውጭ የፋይናንስ ጥገኝነት በመላቀቅ የውስጥ የገቢ አቅሟን በአግባቡ መጠቀም ይጠበቅባታል
Jul 28, 2026 376
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ዘላቂ ልማቷን ለማረጋገጥ ከውጭ የፋይናንስ ጥገኝነት ተላቃ የውስጥ የገቢ አቅሟን በአግባቡ መጠቀም እንዳለባት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ዋና ፀሀፊ ክሌቨር ጋቴቴ ገለጹ። 49ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ይከናወናል። የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ ኤድዋርድ ቢዚማና፣ የአባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ዲፕሎማቶች እና ሌሎች እንግዶች በስብሰባው መክፈቻ ላይ ተገኝተዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ዋና ፀሀፊ ክሌቨር ጋቴቴ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የጂኦፖለቲካ ውጥረቶች፣ የግጭቶች መበራከት፣ የብድር ክፍያ ጫና እና የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት በአህጉሪቷ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ ይገኛሉ። እነዚህን ፈተናዎች ለመወጣት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን አባል ሀገራት የታክስ ስርዓታቸውን እንዲያዘምኑ ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የሀገር ውስጥ ካፒታል ገበያዎችን እንዲያጠናክሩ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። አህጉሪቷ በየዓመቱ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ሳቢያ በርካታ ገንዘብ እንደምታጣና የታክስ መሰብሰብ አቅሟም ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርቷ 16 በመቶ ብቻ መሆኑን አመልክተው፤ ይህ አሰራር በአስቸኳይ መለወጥ እንዳለበትም ተናግረዋል። በግብርና፣ በኃይል፣ በኢንዱስትሪ እና በአየር ንብረት መከላከል የተቀናጀ ፖሊሲና አሰራር መከተል እንደሚገባ ገልጸዋል። የሀገር ውስጥ ቁጠባና ኢንቨስትመንትን ለአህጉሪቱ ልማት ማዋል እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ማሸሽን መግታት እንደሚገባ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ እርስ በርስ ንግድ 17 በመቶ ብቻ ሲሆን፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ሙሉ በሙሉ ሲተገበር በ2045 የውስጥ ንግድን እንደሚያሳድግ ተናግረዋል። የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፣ የመረጃ ስርዓቶችን ለማዘመንና ዲጂታል መሠረተ-ልማቶችን ለማስፋፋት መዋዕለ-ነዋይ ማፍሰስ እንደሚገባም ገልጸዋል።
ሐተታዎች
ከሀገር አቀፍ ንቅናቄ እስከ ዓለም አቀፍ እውቅና፦የአረንጓዴ አሻራ ውጤታማ አበርክቶ
Jul 30, 2026 302
በታዋቂ ዓለም አቀፍ የሳይንስ መጽሔቶች ላይ የታተሙ ተከታታይ ጥናቶች የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር በደን መልሶ ማልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተዕፅኖን በመከላከል ፣ የካርበን ክምችት በማሳደግ እና በማህበረሰብ ተሳትፎ ረገድ ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ መሆኑን አረጋገጡ። የጥናቱ ግኝቶች ከስምንት ዓመታት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)አነሳሽነት የተጀመረው የአረጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር፣ በአፍሪካ ግዙፍ እና እጅግ ውጤታማ ወደሆነ የመሬት ገጽታ መልሶ ማልማት ፕሮግራም ማደጉን የሚያሳይ ጠንካራ ሳይንሳዊ ማስረጃ አቅርበዋል። ኔቸር ፖርትፎሊዮ (Nature Portfolio)፣ ኤልሴቪየር (Elsevier) እና ስፕሪንገር (Springer)ን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባላቸው አሳታሚዎች እ.ኤ.አ. በ2026 የወጡ አምስት ጥናቶች፤ የሳተላይት ምስሎችን፣ የመስክ የዳሰሳ ጥናቶችን፣ የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂዎችን እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም የመርሐ-ግብሩን አካባቢያዊ ፋይዳ ገምግመዋል። ከፍተኛ የችግኝ ጽድቀት ምጣኔ - የውጤታማ መልሶ ማልማት ማሳያ በኤልሴቪየር 'ትሪስ፣ ፎረስስ ኤንድ ፒፕል' (Trees, Forests and People) መጽሔት ላይ የታተመ ጥናት (አሰፋ እና ሌሎች፣ 2026) እንዳመለከተው፣ በደቡብ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የተተከሉ የዛፍ ችግኞች 80 በመቶ የሚገመት የጽድቀት ምጣኔ አስመዝግበዋል፤ ይህም ከሌሎች በርካታ ሰፊ የደን ልማት ፕሮግራሞች ልቆ የተገኘ ነው። ተመራማሪዎቹ ለዚህ ስኬት በዋነኛነት የጠቀሷቸው የተሻሻሉ የመልሶ ማልማት ልምዶችን ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል በዋናው የክረምት ወቅት መትከል፣ ጥንቃቄ የተሞላበት የቦታ ምርጫ፣ እንዲሁም በቴክኒክ ስልጠና የታገዘ ጠንካራ ማህበረሰብ አቀፍ እንክብካቤ ይገኙበታል። የጥናቱ መሪ ዶ/ር ታደሰ አሰፋ እንደገለጹት፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ከሳይንሳዊ የደን አያያዝ ጋር ማቀናጀት አዳዲስ ተከላ የተካሄደባቸው አካባቢዎች ጊዜያዊ የችግኝ መትከያ ቦታዎች ብቻ ሆነው ከመቅረት ይልቅ ዘላቂ ወደሆነ ደንነት እንዲያድጉ አስችሏል። የማህበረሰብ ተሳትፎ ለስኬቱ ሞተር ነው በስፕሪንገር 'ዲስከቨር ኢንቫይሮመንት' (Discover Environment) ላይ የታተመ ሌላ ጥናት ደግሞ ሰፊው የማህበረሰብ ተሳትፎ የመርሐ-ግብሩ ታላቅ ጥንካሬ መሆኑን አመልክቷል። የጥናቱ መሪ ዶ/ር አብዱረዛቅ ሀጂ እንዳስገነዘቡት፣ እያደገ የመጣው የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ እና በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ የህዝብ ተነሳሽነት፣ አባወራዎች ችግኝ መትከልን የአካባቢን የመቋቋም አቅም ለመገንባት፣ ለዘላቂ ግብርና እና ለወደፊት የኑሮ መሰረት እንደተደረገ ኢንቨስትመንት እንዲመለከቱት አድርጓል። የህዝብ ተሳትፎ የመርሐ-ግብሩ የረጅም ጊዜ ስኬት የማዕዘን ድንጋይ መሆኑን ጥናቱ በማጠቃለያው አስቀምጧል። የደን ሽፋን ማደግ የአካባቢን አየር ንብረት ያሻሽላል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ቡኖ በደሌ ዞን የተካሄደ ጥናት በስድስት ዓመታት ውስጥ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን፣ ማለትምከ27.64 በመቶ ወደ 38.24 በመቶ ከፍ ማለቱን አስመዝግቧል። ጥናቱ የመሬት ገጽ የሙቀት መጠን እስከ 1.16 ዲግሪ ሴልሺየስ መቀነሱን ያረጋገጠ ሲሆን፣ ይህም የደን ሽፋን መስፋፋትየአካባቢውን አየር ንብረት እያሻሻለ እና የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅምን እያጠናከረ መሆኑንያሳያል። እነዚህ ለውጦች የስነ-ምህዳር አገልግሎቶችን እንደሚያሳድጉ እና የግብርና ምርታማነትን እንደሚደግፉ ይጠበቃል ሲሉ ተመራማሪዎቹተናግረዋል። ጥናቶች ከፍተኛ የካርበን ክምችት አቅም መኖሩን አጉልተዋልበኔቸር ፖርትፎሊዮ (Nature Portfolio) ሥር በ'ሳይንቲፊክ ሪፖርትስ' መጽሔት ላይየወጣ ሌላ ጥናት፣ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የዛፍ ዝርያዎች እና የግብርና-ደን ሥርዓቶች ከፍተኛ መጠንያለው የካርበን ዳይኦክሳይድ ክምችት የመያዝ አቅም እንዳላቸው አረጋግጧል። አንዳንድ መልመው ያገገሙ መሬቶች በሄክታር ወደ 500 ሜጋግራም የሚጠጋ የካርበን ዳይኦክሳይድ መጠን የያዙ መሆናቸው የተረጋገጠሲሆን፣ ይህም መርሐ-ግብሩ የአየር ንብረት ለውጥን በማቃለል ረገድ ያለውን ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያሳያል። የደን መልሶ ማልማት ስራውን ማስፋፋት የኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት እርምጃ ተሳትፎ የበለጠ እንደሚያጠናክርናበማደግ ላይ ባለው የዓለም አቀፍ የካርበን ገበያ ላይ ዕድሎችን እንደሚፈጥር ተመራማሪዎቹ ገልጸዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የደን ዕድገቱ እንደሚቀጥል ተንብዮአል ማሽን ለርኒንግ፣ የሳተላይት ምስሎች እና የጂኦስፓሻል ትንታኔዎችን በመጠቀም በስፕሪንገር 'ኢንቫይሮመንታል ሞኒተሪንግ ኤንድአሴስመንት' (Environmental Monitoring and Assessment) መጽሔት ላይ የታተመ ሌላ ጥናት እንዳመላከተው፣አሁን ያለው የመልሶ ማልማት ጥረት ከተቀጠለ የኢትዮጵያ የደን ሽፋን ቢያንስ እስከ 2035 ድረስ መስፋፋቱን እንደሚቀጥልተንብዮአል። በመሬት ገጽታ መልሶ ማልማት ላይ የሚደረገው ተከታታይ ኢንቨስትመንት የደን ሽፋንን የበለጠ እንደሚያሳድግ፣ የካርበን ክምችትንእንደሚያጠናክር እንዲሁም የኢትዮጵያን የአየር ንብረት እና የዘላቂ ልማት ግቦችን እንደሚደግፍ ጥናቱ ያሳያል። ዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ እውቅና በአጠቃላይ ሲታይ፣ አምስቱ ገለልተኛ ጥናቶች የኢትዮጵያን አረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ሁለንተናዊ ሳይንሳዊ ግምገማ በማቅረብ፤በደን መልሶ ማልማት፣ በካርበን ክምችት፣ በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም እና በህዝብ ተሳትፎ ረገድ የሚለኩና ተጨባጭ ውጤቶችንማምጣቱን ደምድመዋል። እነዚህ ግኝቶች የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የሰፊ ሥነ-ምህዳር መልሶ ማልማት ቀዳሚ ሞዴል በማድረግ ያስቀመጡትሲሆን፤ ዘላቂ የፖለቲካ ቁርጠኝነት፣ ሳይንሳዊ ዕቅድ እና አገር አቀፍ የህዝብ ንቅናቄ እንዴት ተጨባጭ የአካባቢ ጥበቃ ውጤቶችንማምጣት እንደሚችሉና፣ ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ እና የመሬት መራቆትን ለመከላከል ለሚደረጉ ጥረቶች ከፍተኛ አስተዋጽዖእንደሚያበረክቱ በጉልህ አሳይተዋል።
የበጋ መስኖ ስንዴ፤ የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ የግብርና ዘርፍ እመርታ!!
Jul 28, 2026 458
በሚኪያስ ጎቡ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ወሳኝ አምድ፣ ሕዝብ የኑሮ መሠረትና የምግብ ዋስትና ማዕዘን ነው። በኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ግብርና ዋነኛ የኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት ሆኖ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት ግብርናን ከኢንዱስትሪ፣ ከማዕድን፣ ከቱሪዝም እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር በመጣመር ወሳኝ የዕድገት ምሰሶ የሚሆንበትን ዕድል ፈጥሯል። ይህም በሰብል፣ በእንስሳት እና በሌሎች ዘርፎች እመርታዊ ውጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል። በዚህ ዘርፍ ከተመዘገቡ አስደናቂ ለውጦች መካከል የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አዲስ የዕድገት ፍኖት ከፍቷል። ለዓመታት ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚያስፈልገውን ስንዴ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ስታስገባ የነበረችው ኢትዮጵያ፤ በስትራቴጂካዊ የግብርና ማሻሻያዎች፣ በመስኖ ልማት ማስፋፋት፣ በሜካናይዜሽን እና በአርሶና አርብቶ አደሮች አደረጃጀት የስንዴ ምርቷን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችላለች። ይህ ለውጥ የገቢ ምርትን ከመተካት ባሻገር በምግብ ራስን መቻል፣ ለውጭ ንግድ አቅም እና ለማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት አዲስ ዕድል ፈጥሯል። የስንዴ ምርታማነትም በአርሶና አርብቶ አደሩ ዘንድ የይቻላል መንፈስን በማጎልበት የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ አቅም ፈጥሯል። ከዚህም በተጨማሪ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥርዓት በመገንባት ለአፍሪካና ለቀጣናው ሀገራት የልማት ተሞክሮ አስገኝቷል። የምርትና የምርታማነት አብዮት በክረምት ዝናብ ላይ ብቻ ተንተርሶ የቆየው የኢትዮጵያ ግብርና አሁን ዘመናዊ የአመራረት ምኅዋር ውስጥ ገብቷል። ይህም በቆላማ፣ በደጋማ እና በወንዝ ዳርቻ የሚገኙ ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን ወደ ምርታማ የስንዴ ማሳዎች ቀይሯል። የስንዴ ምርታማነት አብዮትም በመስኖ፣ በሜካናይዜሽን፣ በተሻሻሉ የአመራረት ዘዴዎች እና በአርሶና አርብቶ አደሮች የተቀናጀ ጥረት የምርታማነትን ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ አሻሽሏል። በዚህም ኢትዮጵያ ከውጭ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የምታስገባውን ስንዴ በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት ወደ ውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥሯል። ይህ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የግብርናን ገጽታ የቀየረ የምርትና የምርታማነት አብዮት ነው። ፖሊሲ፣ ቴክኖሎጂ፣ መስኖ እና የአርሶና አርብቶ አደሩ ትጋት ሲጣመሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁለንተናዊ ብልፅግናን የሚያጎናጽፍ አቅም መፍጠር እንደሚቻል የሚያሳይ የልማት ተሞክሮ ሆኗል። የክላስተር ግብርና፤ የሜካናይዜሽን ስኬት እመርታ!! የኢትዮጵያ የስንዴ ልማት ስኬት ከውጤታማ የአሠራር ዘዴዎች መካከል የክላስተር ግብርናና የሜካናይዜሽን አጠቃቀም ዋነኛ ምሰሶዎች ናቸው። ባለአነስተኛ ይዞታ አርሶ አደሮችን በማደራጀት ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያ እና የሰብል ጥበቃ ግብዓቶችን በወቅቱና በተደራጀ መንገድ እንዲያገኙ አስችሏል። የሜካናይዜሽን መስፋፋት ባህላዊ በሰው ጉልበትና በእንስሳት ኃይል የተመሠረተውን አሠራር በዘመናዊ ማሽነሪዎች በመተካት የማሳ ዝግጅትን፣ የዘር አዘራርን እና የምርት አሰባሰብን ውጤታማ አድርጓል። ትራክተርና ኮምባይነር አጠቃቀም የጊዜና የጉልበት ብክነትን ከመቀነሱ ባሻገር በምርት ስብሰባ ወቅት የሚደርሰውን ብክነት በመቀነስ የምርት ጥራትና መጠን እንዲጨምር አስችሏል። የክላስተር ግብርናና የሜካናይዜሽን ሥርዓት የኢትዮጵያን የስንዴ ልማት ከተለመደው የኑሮ ግብርና ወደ ተወዳዳሪ የንግድና የኢንዱስትሪ ግብዓት ምንጭነት እንዲሸጋገር በማድረግ ትልቅ ለውጥ አምጥቷል። የማክሮ ኢኮኖሚ አወንታዊ ተፅዕኖ፡- የኢትዮጵያ የስንዴ ልማት ባለፉት ጥቂት ዓመታት በሀገሪቱ ማክሮ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ለውጥ አምጥቷል። በተለይም የበጋ መስኖ ስንዴ ምርት መስፋፋቱ ከውጭ የሚገባውን ስንዴ በመተካት የምግብ ራስን የመቻል ግብን እያሳለጠ ይገኛል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከስንዴ አስመጪነት ወደ ላኪነት መሸጋገሯ የንግድ ሚዛንን በማሻሻል ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ እንዲፈጠር ዕድል ከፍቷል። በሌላ በኩል የስንዴ ምርት መጨመሩ የምግብ አቅርቦትን በማረጋጋትና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። ይህም የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን በማጎልበት የአርሶና አርብቶ አደሩን ምርታማነት የበለጠ ለማጠናከር እያስቻለ ነው። የይቻላል ተምሳሌቱ፤ የበጋ ስንዴ ምርታማነት፡- የኢትዮጵያ የስንዴ ልማት የግብርና ስኬት ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰብ አብዮትም ነው። ለዘመናት ስንዴን ከውጭ ማስገባት የማይቀር የሚመስለውን እሳቤ በመስበር ከጥገኝነት የመላቀቅ መንፈስን አጎልብቷል። በመስኖ የተደገፈ ዓመቱን ሙሉ የማምረት ባህልን በማስፋፋትም ለሌሎች የግብርናና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተነሳሽነት ፈጥሯል። ከአፍሪካ ቀዳሚነት ወደ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ፡- የስንዴ ልማቱ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት የሚያረጋግጥ አቅም በመፍጠር በአፍሪካ ቀዳሚ አምራች ሀገር አድርጓታል። የመስኖ ልማት መስፋፋትና ቆላማ አካባቢዎችን ወደ ምርታማ የስንዴ ማሳዎች መቀየር ለኢኮኖሚው ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ለአፍሪካ የተግባር ምሳሌ፡- የኢትዮጵያ ተሞክሮ ለምሥራቅ አፍሪካና ለመላው አህጉሪቱ በምግብ ራስን መቻል እንደሚቻል በተግባር አሳይቷል። የውጭ የስንዴ ገቢ ምርት ጥገኝነትን በማስቀረት በአፍሪካ ምድር የምግብ ሉዓላዊነት ሊረጋገጥ እንደሚችል ተጨባጭ ውጤት አሳይቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ መድረኮች እንደገለጹት፤ ከስንዴ እርዳታና ከውጭ ጥገኝነት መላቀቅ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በሀገር ውስጥ ምርት ማረጋገጥ እና መሬትና የመስኖ ውኃን በአግባቡ በመጠቀም ኢትዮጵያን ከምርት ተቀባይነት ወደ አምራችነትና ወደ ላኪነት ማሸጋገር እየተቻለ ነው። ማጠቃለያ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በኢትዮጵያ የተመዘገበ የግብርና ስኬት ብቻ አይደለም፤ የአስተሳሰብ፣ የፖሊሲ፣ የቴክኖሎጂ እና የሀገራዊ ቁርጠኝነት ፍሬ የሆነ የልማት አብዮት ነው። ለዘመናት የውጭ ጥገኝነት ምልክት ሆኖ የቆየውን የስንዴ አቅርቦት ችግር በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት ኢትዮጵያ ከአስመጪነት ወደ ላኪነት የምትሸጋገርበትን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍታለች። ይህ ስኬት የአንድ የግብርና ፕሮጀክት ውጤት ብቻ ሳይሆን መሬትን፣ ውኃን፣ ሳይንስን፣ ቴክኖሎጂን እና የአርሶ አደሩን ትጋት በአንድ ራዕይ ያስተሳሰረ የብልፅግና ሞዴል መሆኑን አሳይቷል። በተለይም የክላስተር ግብርና፣ የመስኖ ልማት፣ የሜካናይዜሽን መስፋፋት እና የተሻሻሉ የምርት ቴክኖሎጂዎች ተቀናጅተው ሲተገበሩ ግብርና በአጭር ጊዜ ውስጥ የሀገር ኢኮኖሚን የመቀየር አቅም እንዳለው በተግባር አረጋግጧል። ከዚህ በኋላ የሚጠበቀው ይህንን ስኬት በማስቀጠል የጥራት ማሻሻያን፣ የእሴት ጭማሪ ኢንዱስትሪዎችን፣ የውጭ ገበያ ተወዳዳሪነትን እና የግብርና ዲጂታላይዜሽንን በማጠናከር ስንዴን ከምግብ ዋስትና ባሻገር የውጭ ምንዛሬ፣ የኢንዱስትሪ ግብዓት እና የሀገራዊ ኢኮኖሚ መረጋጋት ስትራቴጂያዊ ምሰሶ ማድረግ ነው። የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የኢትዮጵያን ይቻላል መንፈስ በማሳየት የምግብ ራስን መቻልን ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን፣ የውጭ ምንዛሬ አቅምን፣ የአፍሪካ የልማት ተምሳሌትነትን እና የቀጣይ ትውልድ የብልፅግና መሠረትን እየገነባ ነው። በዚህም የተገኘው የግብርና ድል የአንድ ወቅት የምርት ጭማሪ ሳይሆን የኢትዮጵያን የዕድገት ታሪክ የሚቀይርና ለአፍሪካም አዲስ የልማት አድማስ የሚከፍት ዘላቂ ስኬት ሆኖ ይቀጥላል።
የባሕር በር ፣ የኢትዮጵያውያን የልማትና የሕልውና ጥያቄ
Jul 26, 2026 425
የባሕር በር ፣ የኢትዮጵያውያን የልማትና የሕልውና ጥያቄ በዜናው ፈንቴ እንደ መግቢያ፡- የባሕር በር የአንድ ሀገር የውኃ ዳርቻ ባለቤትነት መገለጫ ብቻ አይደለም፤ የንግድ ደም ስር፣ የኢኮኖሚ አምድ፣ ፍኖተ ስልጣኔ፣ የባህል መስተጋብርና የጂኦፖለቲካ ኃይል እንጂ። የዓለም ታላላቅ የሥልጣኔ መሰረት የሆኑ ከተሞች የውኃማ አካላትን ጠርዝ ተንተርሰው የተቆረቆሩ ናቸው። ባሕር የውሃ ስፋት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ የንግድ ማሳለጫ፣ የደህንነት ዋስትና የሉዓላዊነት ማረጋገጫ ነው። የዓለም 80 በመቶ የንግድ ልውውጥ በባህር ላይ ይከወናል፤ በዓመቱ በአማካኝ እስከ 12 ቢሊዮን ቶን ጭነት ይጓጓዛል፤ የባሕር በር ያላቸው ሀገራት በፈጣን ዕድገት፣ በወጭ ንግድ፣ በኢንዱስትሪ መስፋፋትና በቀጣናዊ ተፅዕኖ የተሻለ አቅም መገንባት ይችላሉ፤ የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት ደግሞ ለከፍተኛ የሎጂስቲክስ ወጪ፣ ለንግድ መጓተትና ለውጭ ጥገኝነትን ይጋለጣሉ፡፡ ለዚህም ነው የባሕር በር የአንድ ሀገርና ዜጎች የህልውና ጉዳይ ነው የሚባለው። ይህ እውነታ በኢትዮጵያ በግልጽ ይንጸባረቃል፤ በአፍሪካ ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ያላት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ በኃይል ልማትና በዲጂታል ኢኮኖሚ እየተለወጠች ነገር ግን የባሕር በር የሌላት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት። ተለዋዋጭ በሆነው የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ትልቅ የሕዝብ ቁጥርና በፍጥነት እያደገ ያለ ኢኮኖሚ ለምትመራው ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባሕር በር ማግኘት የህልውና ፍትሕ እንጂ ቅንጦት አይደለም፡፡ ለቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ልማትም ዋስትና። ቀይ ባሕር አውሮፓን፣ ኤዥያና አፍሪካን የሚያገናኝ፤ የስዌዝ ቦይን ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር የሚያስተሳስር፣ የዓለምን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያሳልጥ የዓለም ወሳኝ የባሕር መስመር ነው። በዚህ ወሳኝ ጂኦ ስትራቴጂክ ቀጣና የሚገኝ ሀገር አስተማማኝ የባሕር በር ያስፈልገዋል። ኢትዮጵያም ይገባታል፤ የታሪክ፣ የጂኦግራፊ፣ ነባራዊ ሁኔታና የተፈጥሮ ሚዛን ወደ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ያጋደለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ለሺህ ዘመናት የተሻገረ በአክሱም ስልጣኔ ዓለምን የናኘ ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ እንደነበራት የአደባባይ ሐቅ ነው። የአዱሊስ ወደብም አፍ አውጥቶ ይናገራል፤ ከመካከለኛው ዘመን እስከ ቅርቡ አሰብ ወደብ ኢትዮጵያና የባሕር በር የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ሆነው ቆይተዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሲቪልና የአካባቢ ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህር በለጠ ብርሃኑ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ከዓባይና የቀይ ባሕር ውሃዎች ጋር የተቆራኘ መሆኑን ያስታውሳሉ፡፡ የባሕር በር የሀገር ብሔራዊ ጥቅም አንጓ ሆኖ እያለ ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር የተገለለችበት መንገድ የሚያስቆጭና በሀገር ሉዓላዊነት ላይ የተፈፀመ በደል ነው ይላሉ። የኢትዮጵያ የወቅቱ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና መልክዓ-ምድራዊ ማስረጃዎች እንዳሉት ያብራራሉ። ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት ተመራጭ መንግሥትና ሕጋዊ የሕዝብ ውክልና ያልተሰጠው የሽፍታ ስብስብ ኤርትራን በማስገንጠል ኢትዮጵያን የባሕር በር አልባ አድርጓታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ይህንን ሕገ ወጥና በሀገር ላይ የተፈጸመ ክህደት ሲያብራሩ "ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበትን ውሳኔ ማን ወሰነው?" ሲሉ ይጠይቃሉ። ሲቀጥሉም "ካቢኔው ይሆናል ብለን የካቢኔውን ዶክመንት ብናነብ የለም፣ ካቢኔው አያውቅም። አይ የለም ምክር ቤት ይሆናል የወሰነው ብለን ብንወስድ ምክር ቤትም አልነበረም፣ ምክር ቤቱም አላወቀም። የለም የኢትዮጵያ ህዝብ በሪፈረንደም ወስኖ ይሆናል እንዳይባል አልወሰነም፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልወሰነውን፣ ተወካዮቹ ያላዩትን፣ ቢያንስ ቢያንስ አስፈጻሚው ካቢኔ ያላየውን ውሳኔ ማን ወሰነው? ማጣትን የሚያክል ነገር ያጣንበት መንገድ ሕጋዊነት ችግር እንዳለው የሚያሳየው፣ ተቋሞች አልገቡበትም" በማለት ውሳኔው ሕዝባዊና ተቋማዊ ውክልና ባልነበረው ስብስብ የተወሰነ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የሀገር ውስጥ ባንዳና ከውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በፈጠሩት ጥምረት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ኢ-ፍትሐዊ በደል ፈፅመዋል። ይህም ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት፣ በፍጥነት እያደገች ያለች ኢኮኖሚ ያላትና በቀጣናው የሰላምና የደኅንነት ዋና ተዋናይ የሆነችውን ኢትዮጵያ ያላቋረጠ የጂኦፖለቲካ ፈተና ውስጥ አስገብቷታል። በዚህ አውድ ውስጥ የቀረበው የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሌላ ሀገርን ግዛት ለመውሰድ ወይም ሉዓላዊነትን ለመጋፋት የቀረበ ጥያቄ አይደለም። ይልቁንም በሰላማዊ ውይይት፣ በጋራ ጥቅም፣ በቀጣናዊ ትብብር እና በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች መሠረት ሁሉንም ወገኖች የሚጠቅም ዘላቂ መፍትሔ ለማስገኘት የቀረበ የልማትና የሕልውና አጀንዳ ነው። የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ ከኢኮኖሚ ጥቅም በላይ የሀገር ዘላቂ ዕድገት፣ የቀጣናው ትስስር እና የብሔራዊ ሕልውና ጉዳይ ነው። ስለዚህም ጥያቄው ታሪካዊ እውነታን፣ ሕጋዊ መሠረትን፣ ጂኦግራፊያዊ እውነታን እና የጋራ ቀጣናዊ ጥቅምን በሚያጣምር መንገድ መታየት ያለበት ስትራቴጂካዊ ጉዳይ እንጂ የግጭት ወይም የመስፋፋት የፖለቲካ መገለጫ ተደርጎ የሚወሰድ አይደለም። 👉ባሕር፤ የታሪካችን አካል፣ የወደፊታችንም መሠረት የኢትዮጵያ ከባሕር ጋር ያላት ትስስር ከዛሬ የተጀመረ ሳይሆን ከሥልጣኔዋ መነሻ ጋር የተቆራኘ የአደባባይ ሐቅ ነው። የአክሱም ሥልጣኔ በአዱሊስ ወደብ በኩል ከሮማ፣ ከግብፅ፣ ከሕንድ፣ ከዓረቡ ዓለምና ከሩቅ ምሥራቅ ጋር የንግድና የሥልጣኔ ትስስር መፍጠሩ በታሪክ የተመዘገበ እውነታ ነው። በዚህ ወደብ አማካኝነት ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ቅመማ ቅመሞችና ሌሎች የንግድ ሸቀጦች ወደ ዓለም ገበያ ይደርሱ እንደነበርም ታሪክ ያስረዳል። በዚህ ረገድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኃይድሮ ፖለቲክስ ተመራማሪና ዓለም አቀፍ የውሃ ተደራዳሪ ያዕቆብ አርሳኖ (ዶ/ር) እንደሚገልጹት፣ የባሕር በር ጉዳይ በኢትዮጵያ ታሪክ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው የብሔራዊ ጥቅም ማጠንጠኛ ነው። ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ ከባሕር ጋር የነበራት ታሪካዊ ትስስር በተለያዩ የፖለቲካ ለውጦች ቢቋረጥም፣ በሕዝብ የልብ ማህደረ ውስጥ ያለው ስፍራ አልተሸረሸረም። ኢትዮጵያ በታሪኳ አሰብን፣ ምጽዋንና ሌሎች ወደቦችን ተጠቅማ ከቀጣናውና ከዓለም ጋር ሰፊ የንግድ ትስስር የፈጠረች ሀገር ናት። ስለዚህ የባሕር በር ጉዳይ አዲስ ፍላጎት ወይም አዲስ ፖለቲካዊ አጀንዳ ሳይሆን ከሀገሪቱ ታሪክ፣ ኢኮኖሚና ጂኦግራፊያዊ እውነታ ጋር የተቆራኘ ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው። ዛሬ ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በአቪዬሽን፣ በዲጂታል ኢኮኖሚና በኃይል ልማት ዘርፎች ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች ትገኛለች። ይሁን እንጂ ይህ የኢኮኖሚ መስፋፋት ውጤታማ የሎጂስቲክስ ሥርዓትና የተረጋጋ የባሕር በር ተደራሽነት ካልተደገፈ ሙሉ አቅሙን ማሳየት አይችልም። በዚህ ምክንያት የባሕር በር ጉዳይ የታሪክ ትውስታ ብቻ ሳይሆን፣ የዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ብልጽግና መሠረት ሆኗል። በመሆኑም የባሕር በር ጉዳይ የትናንትን ታሪክ ለመመለስ ብቻ ሳይሆን፣ የነገዋን ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለማጠናከር፣ የንግድ ወጪዎችን ለመቀነስ፣ የቀጣናዊ ትብብርን ለማስፋትና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያገለግል ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው። ከዚህ አንጻር በቀይ ባሕር አካባቢ በቅርብ ርቀት የምትገኘው ኢትዮጵያ ከባሕር ተደራሽነት ውጭ መሆኗ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገትና በቀጣናዊ ተወዳዳሪነት ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ በተረጋጋ የውይይትና የትብብር መንገዶች መፍትሔ የሚሻ ስትራቴጂክ ጉዳይ መሆኑን ያሳያል። 👉የባሕር በር፤ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ የልማትና የሕልውና ጥያቄ በ21ኛው ክፍለ ዘመን የአንድ ሀገር ጥንካሬ በወታደራዊ ኃይል ብቻ ሳይሆን፣ በኢኮኖሚ ተወዳዳሪነት፣ በንግድ ትስስር፣ በሎጂስቲክስ ቅልጥፍናና ዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነት ይለካል። በዚህ መለኪያ የባሕር በር ለኢትዮጵያ የቅንጦት ሳይሆን የልማት መሠረታዊ መስፈርት ሆኖ ይታያል። በዚህ አውድ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ታሪካዊ እውነታን፣ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥንና ዓለም አቀፍ የሕግ መርሆዎችን ያጣመረ የልማት ጉዳይ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ። ኢትዮጵያ ለዚህ ጥያቄ መፍትሔ ለማግኘት የምታደርገው ጥረትም በሰላማዊ ውይይት፣ በዲፕሎማሲ፣ በጋራ ጥቅምና በቀጣናዊ ትብብር ላይ የተመሠረተ ነው። ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት፣ በአፍሪካ በፍጥነት እያደገች ያለች፣ በአቪዬሽን፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በኃይልና በዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየገነባች ያለች ኢትዮጵያ፣ ይህን የልማት እመርታ በተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ሥርዓትና በተረጋጋ የባሕር በር ተደራሽነት ካልደገፈች ሙሉ አቅሟን ማሳካት አትችልም። በዚህ ምክንያት የባሕር በር ጉዳይ የአንድ ወደብ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን፣ የንግድ ተወዳዳሪነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ብልፅግና ጉዳይ ነው። እንደዚሁም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ደጋግመው እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ ጥያቄ የጦርነት ወይም የመስፋፋት ሳይሆን፣ በሰላማዊ ውይይት፣ በጋራ ጥቅምና በቀጣናዊ ትብብር መሠረት መፍትሔ የሚፈልግ የልማትና የሕልውና ጉዳይ ነው። 👉የኢኮኖሚ እመርታና የባሕር በር ትስስር በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ኢትዮጵያ በብዝኅ ኢኮኖሚ ሥርዓት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና ዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፎች መሠረታዊ ለውጦችን አስመዝግባለች። የግብርና ምርት ጨምሯል፣ የኢንዱስትሪ ማምረት አቅም ጎልብቷል፣ የማዕድን ሀብቶች ወደ ውጭ ገበያ እየቀረቡ ሲሆን፣ የቱሪዝምና የዲጂታል ኢኮኖሚ መስፋፋትም አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ከፍቷል። ይሁን እንጂ ይህ እመርታ ተወዳዳሪና ዘላቂ ሊሆን የሚችለው ከተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ሥርዓትና ከአስተማማኝ የባሕር በር ተደራሽነት ጋር ሲተሳሰር ነው። የግብርና ምርቶች፣ የኢንዱስትሪ ውጤቶች፣ የማዕድን ሀብቶችና ሌሎች ወደ ዓለም ገበያ በፍጥነትና በወጪ ቆጣቢነት እንዲደርሱ የባሕር በር ወሳኝ ሚና ይጫወታል። የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) እንደሚገልጹት፣ የኢትዮጵያና የቀይ ባሕር ትስስር ከሀገረ መንግሥቷ ታሪክ ጋር የተቆራኘ ሲሆን፣ የባሕር በር ጉዳይም የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የብሔራዊ ጥቅም ቁልፍ አጀንዳ ነው። በተለይም ኢትዮጵያ በየዓመቱ ለወደብና ለሎጂስቲክስ አገልግሎት ብቻ ከ1.5 እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓ፣ የባሕር በር ጉዳዩ ከኢኮኖሚ ጋር ያለውን ቀጥተኛ ትስስር ያሳያል። የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎችም እንደሚጠቁሙት፣ አስተማማኝ የባሕር በርና አማራጭ የወደብ አገልግሎት ለኢትዮጵያ ቅንጦት ሳይሆን የፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገቷን ለማስቀጠል የሚያስፈልግ መሠረታዊ ፍላጎት ነው። ስለዚህ የባሕር በር ጉዳይ የአንድ ዘርፍ ፍላጎት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን፣ የንግድ መስፋፋትንና የዘላቂ ብልጽግና ጉዞን የሚወስን ስትራቴጂካዊ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ነው። 👉ከታሪካዊ መብት ወደ የጋራ ብልፅግና፤ ምላሽ የሚሻው የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ!! የኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ የትናንትን ታሪክ ለማስታወስ ብቻ የቀረበ አይደለም፤ የነገውን የቀጣናው ኢኮኖሚ፣ የንግድ ትስስርና የጋራ ብልፅግና የሚወስን ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ሀገራት ፉክክርን ሳይሆን ትብብርን ከመረጡ፣ ወደቦች የአንድ ሀገር ብቻ ሳይሆኑ የቀጣናውን የጋራ ዕድገት ማስፈንጠሪያ መድረኮች ይሆናሉ። በዚህ እሳቤም የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለቀይ ባሕር ቀጣና፣ ለአፍሪካ ቀንድ እና ለቀጣናዊ ሰላምና ኢኮኖሚያዊ ትስስር አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት የሚያስችል ዕድል ነው። የምጣኔ ሀብት ምሁር ጀማል መሐመድ (ዶ/ር) እንደሚገልጹትም፣ የኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት አስተማማኝ የባሕር በር ተደራሽነትን ይሻል፤ ይህ አለመኖሩ ግን የንግድ ተወዳዳሪነትን በመገደብ በሀገሪቱ ኢኮኖሚና በዜጎች ተጠቃሚነት ላይ ቀጥተኛ ጫና ያሳድራል። ስለዚህ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የግዛት መስፋፋት ሳይሆን፣ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ሀገር ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገቷን ለማረጋገጥ፣ የንግድ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግና የቀጣናዊ የጋራ ብልፅግናን ለማጠናከር የሚቀርብ የልማትና የሕልውና ጥያቄ ነው። 👉የቀይ ባሕር ጂኦፖለቲካ፤ የዓለም ትኩረት ለምን በቀጣናው ላይ ነው? የቀይ ባሕር ከውሃ አካልነቱ ባሻገር የዓለም ኢኮኖሚና የጂኦፖለቲካ ወሳኝ ማዕከል ነው። ከሕንድ ውቅያኖስ እስከ ሜዲትራኒያን የሚዘረጋው ይህ የባሕር መስመር የእስያን፣ የአፍሪካንና የአውሮፓን ኢኮኖሚዎች የሚያገናኝ ዋነኛ የዓለም የንግድ መተላለፊያ ነው። በዚህ ቀጣና የሚያልፉ መርከቦች ሸቀጦችን ብቻ ሳይሆን የኃይል አቅርቦትን፣ የምግብ ዋስትናንና የዓለም ኢኮኖሚ ቀጣይነትንም ይሸከማሉ። ስለዚህም የቀይ ባሕር ደህንነት የአንድ ቀጣና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የዓለም አቀፍ ጉዳይ ሆኗል። በቀጣናው የሚፈጠር ማንኛውም መስተጓጎል የነዳጅና የምግብ ዋጋ፣ የመጓጓዣ ወጪ እንዲሁም የዓለም የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ ያሳድራል፤ ስለዚህ ዓለም የቀይ ባሕርን በልዩ ትኩረት ትከታተላለች። 👉ኢትዮጵያ፤ የቀጣናው ተፈጥሯዊ ማዕከል ኢትዮጵያ ለሦስት አስርት ዓመታት ከቀይ ባሕር ዳርቻ ተገልላ ብትቆይም፣ የቀጣናው ትልቁ ኢኮኖሚ፣ ገበያና የሰው ኃይል ማዕከል ሆና ቀጥላለች። ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ፣ በፍጥነት እያደገ ያለ ኢኮኖሚ፣ ጠንካራ የአየር መጓጓዣ ትስስር፣ ትልልቅ የኃይል ፕሮጀክቶችና እየሰፋ ያለ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ያላት ሀገር፣ በቀይ ባሕር ጂኦ-ኢኮኖሚ ውስጥ ማዕከላዊ ሚና እንዳይኖራት ማሰብ አይቻልም። በመሆኑም የኢትዮጵያ ፍላጎት ወደ ባሕር መድረስ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጣናው ዘላቂ የኢኮኖሚ ትስስርና የጋራ ብልፅግና የሚያገለግል አስተማማኝና ተመጣጣኝ የባሕር በር ተደራሽነት ማረጋገጥ ነው። ይህም ለጎረቤት ሀገራት የንግድ፣ የኢንቨስትመንት፣ የሥራ ዕድልና የመሠረተ ልማት መስፋፋትን በማፋጠን የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያጠናክር እድል ይፈጥራል። 👉ከታሪክ ወደ የጋራ ጥቅም የቀይ ባሕር ቀጣና በታሪክ ዘመናት የሥልጣኔ፣ የንግድና የባህል መገናኛ ሆኖ ቆይቷል። ከአክሱም ጀምሮ እስከ ዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ድረስ የባሕር በር ከሀገሪቱ ኢኮኖሚና ታሪክ ጋር የተሳሰረ ተፈጥሯዊ አካል ነው። ይህን ታሪክ ማስታወስም ያለፉ ግጭቶችን ለመቀስቀስ ሳይሆን፣ የዛሬውን ጉዳይ በትክክለኛ ታሪካዊ እና ስትራቴጂያዊ አውድ ለመረዳት ነው። በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ከታሪካዊ መብት ባሻገር፣ ከኢኮኖሚ ዕድገት፣ ከሕዝብ ብዛት፣ ከቀጣናዊ ትስስርና ከጋራ ብልፅግና አንፃር ሊታይ ይገባል። ዘላቂ መፍትሔም በዓለም አቀፍ ሕግ፣ በጋራ ጥቅም፣ በኢኮኖሚ ትብብርና በተቋማዊ ውይይት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፣ ለኢትዮጵያም ሆነ ለመላው የቀይ ባሕር ቀጣና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያጎለብት ሊሆን ይገባል። 👉የወደፊቷ ኢትዮጵያ፤ ከብሉ ኢኮኖሚ ጋር የተሳሰረ ርዕይ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ፣ ከዚያም ወደ እሴት ጨማሪ ምርትና ዲጂታል ኢኮኖሚ እየተሸጋገረ ነው። ይህ ሽግግር ዘላቂ እንዲሆን ግን ውጤታማ የሎጂስቲክስ ሥርዓትና አስተማማኝ የባሕር በር ተደራሽነት ወሳኝ ነው። በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ የባሕር በር አጀንዳ የፖለቲካ ክርክር ሳይሆን የትውልድ የልማት ራዕይ ነው። በሕግ፣ በዲፕሎማሲና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ኢትዮጵያን ከዓለም ገበያ በተሻለ ሁኔታ ያገናኛል፤ ለቀጣናውም መረጋጋትና የጋራ ብልፅግና መሠረት ይሆናል። ስለዚህ የባሕር በር ጉዳይ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ዕድገትና የብሉ ኢኮኖሚ የወደፊት ራዕይ አካል ነው። 👉መደምደሚያ፡ የባሕር በር ጉዳይ፤ የግጭት ሳይሆን የጋራ ብልፅግና መንገድ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ያለፈውን ታሪክ ለመመለስ ብቻ የቀረበ ጥያቄ ሳይሆን፣ የወደፊቱን የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ብልፅግና የሚወስን ስትራቴጂያዊ አጀንዳ ነው። የባሕር በር ተደራሽነት የሌላ ሀገር ጥቅምን በመጉዳት ሳይሆን፣ በጋራ ጥቅም፣ በኢኮኖሚ ትብብርና በቀጣናዊ ልማት ላይ የተመሠረተ የዕድገት መንገድ ነው። በ21ኛው ክፍለ ዘመን የሀገራት ብልፅግና በመገፋፋት ሳይሆን በመተባበርና በጋራ ዕድገት ይገነባል። ስለዚህ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ለቀጣናው የኢኮኖሚ ትስስር፣ ለንግድ መስፋፋትና ለዘላቂ ሰላም አዲስ ዕድል የሚከፍት ነው። ከአክሱም ሥልጣኔ ጀምሮ ከቀይ ባሕር ጋር የቆየው ታሪካዊ ትስስር ከዘመኑ የሕዝብ ብዛት፣ ከኢኮኖሚ ዕድገትና ከቀጣናዊ ሚና ጋር ተያይዞ አዲስ ስትራቴጂያዊ አስፈላጊነት አግኝቷል። ስለሆነም አስተማማኝ የባሕር በር ተደራሽነት ማረጋገጥ የዛሬው ትውልድ የልማት ራዕይና የጋራ ኃላፊነት ነው። ይህም በጽኑ ሀገራዊ አንድነት፣ በበሰለ ዲፕሎማሲ፣ በውይይትና በጋራ ጥቅም መርህ ሊመራ ይገባል። በመጨረሻም የባሕር በር የትናንት ትዝታ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ የነገ ብልፅግና፣ የቀጣናው የጋራ ልማትና የአፍሪካ ተስፋ መንገድ ነው። የባሕር በር የኢትዮጵያ የነገ ብልፅግና መንገድ እንጂ የትናንት ትዝታ ብቻ አይደለም!!
ምግቤን ከደጄ፤ የከተማ ግብርና አዲሱ የምግብ ዋስትና መሰረት
Jul 25, 2026 470
በመቅደስ ወልዴ መግቢያ፡- ዛሬ ዓለም በፈጣን የከተሜነት ሽግግር ውስጥ ትገኛለች። በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ከገጠር ወደ ከተማ በመፍለስ፣ ከተሞችን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንትና የኑሮ ማዕከላት እያደረጓቸው ነው። ይህ ሽግግር አዳዲስ የልማት ዕድሎችን ቢፈጥርም፣ ከምግብ አቅርቦት እስከ የኑሮ ውድነት፣ ከአካባቢ ጥበቃ እስከ የሥራ ፈጠራ ድረስ ያሉ አዳዲስ ፈተናዎችንም አስከትሏል። በተለይም በታዳጊ ሀገራት የከተሞች መስፋፋት የምግብ ዋስትናን ከልማት ፖሊሲዎች ማዕከል ላይ አስቀምጦታል። በ2050 ከዓለም ሕዝብ ሁለት ሦስተኛው በከተሞች እንደሚኖር የሚጠበቀው እውነታ፣ ከተሞች ምግባቸውን ለማረጋገጥ አዳዲስና ዘላቂ መፍትሔዎችን እንዲፈልጉ አስገድዷቸዋል። ኢትዮጵያም ከዚህ ዓለም አቀፋዊ ሽግግር ውጭ አይደለችም። የከተማ ነዋሪዎች ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ፣ የምግብ አቅርቦት፣ የገበያ መረጋጋትና የኑሮ ውድነት አዳዲስ የፖሊሲ ጉዳዮች ሆነው ተነስተዋል። በዚህ ዐውድ ውስጥ የከተማ ግብርና ባዶ ቦታን ወደ ምርት፣ ቆሻሻን ወደ ማዳበሪያ፣ ሸማቹን ወደ አምራች የሚቀይር ዘመናዊና ዘላቂ የልማት መንገድ ሆኖ እየጎለበተ ነው። የከተማ ግብርና፤ ምንነቱና ጠቀሜታው የከተማ ግብርና በከተማ ውስጥ በሚገኙ አነስተኛ ቦታዎች፣ በመኖሪያ ግቢዎች፣ በሕንፃ ጣሪያዎችና በበረንዳ ስፍራዎች ላይ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ቀላል የምርት ዘዴዎችን በመጠቀም አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ እንስሳት፣ ዓሳና ሌሎች የግብርና ውጤቶችን የማምረት ሥርዓት ነው። ቀደም ሲል ግብርና የገጠር ብቻ ተደርጎ ይታሰብ የነበረው አመለካከት ዛሬ በእጅጉ ተለውጧል። በከተሞች የሚገኙ ጠባብ ስፍራዎች እንኳን ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የልማት መስኮች ሆነዋል። በቤት ዙሪያ ይደረግ የነበረው ቀላል የጓሮ አትክልት ልማትም ዛሬ ለሺዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ፣ ገበያን የሚያረጋጋና የሀገር ኢኮኖሚን የሚደግፍ ዘርፍ ሆኗል። ከተሞችን ውብና አረንጓዴ ከማድረጉ ባሻገር፣ ነዋሪዎች በራሳቸው ምርት የምግብ ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ፣ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙና ለአካባቢ ጥበቃ ተጨባጭ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ አስችሏቸዋል። እንዲሁም የዶሮ እርባታ፣ የንብ ማነብና ሌሎች አነስተኛ የግብርና ሥራዎች የቤተሰብን ምግብ ከማሟላት ባለፈ ገበያውን በማረጋጋት ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። የከተማ ግብርና ለምን አስፈለገ? የግብርና ልማት ዛሬ በገጠር አርሶ አደሮች ጥረት ብቻ የሚገደብ አይደለም። የከተሞችን እምቅ ሀብት በመጠቀምና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በማቀናጀት የኑሮ ውድነትን መቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና አረንጓዴ ኢኮኖሚን መገንባት የሚቻልበት ውጤታማ መንገድ መሆኑ በተግባር ተረጋግጧል። ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ተሞክሮዎችም የከተማ ግብርና የከተሞችን ገበያ በማረጋጋት፣ ለወጣቶችና ለሴቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የከተማ ቆሻሻን ወደ ተፈጥሯዊ ማዳበሪያ በመቀየርና የከተሞችን አረንጓዴነት በማጎልበት ያለውን ጉልህ አስተዋጽኦ በተግባር አሳይተዋል። የከተማ ግብርና፤ ከጓሮ ልማት ወደ ሀገራዊ የልማት ስትራቴጂ ቀደም ሲል በቤት ጓሮ የሚከናወን ቀላል የአትክልት ልማት ተደርጎ ይታይ የነበረው የከተማ ግብርና፣ ዛሬ የምግብ ዋስትናን፣ የገበያ መረጋጋትን፣ የሥራ ፈጠራንና የአረንጓዴ ኢኮኖሚን የሚያጠናክር ሀገራዊ የልማት ስትራቴጂ ሆኖ ተቀይሯል። በአነስተኛ ቦታዎች፣ በቤት ግቢዎች፣ በሕንፃ ጣሪያዎችና በባዶ መሬቶች ላይ የአትክልት፣ የፍራፍሬ፣ የዶሮ እርባታ፣ የወተት ሀብት፣ የንብ እርባታና ሌሎች የግብርና ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ። "ምግቤን ከደጄ" የሚለው ሀገራዊ ንቅናቄም የከተማ ነዋሪዎች በራሳቸው ምርት የምግብ ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ አዲስ ዕድል ፈጥሯል። የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ እስከ የገበያ መረጋጋት የከተማ ግብርና ከሚያስገኛቸው ትልልቅ ጥቅሞች መካከል ዋነኛው የምግብ ምርትን ለተጠቃሚው በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ወጪና በተሻለ ጥራት ማድረስ መቻሉ ነው። በከተማ ውስጥ የሚመረቱ አትክልቶች፣ ፍራፍሬዎች፣ እንቁላልና ወተት ረጅም ርቀት ሳይጓዙ በቀጥታ ለገበያ ስለሚቀርቡ ትኩስነታቸውን ይጠብቃሉ፤ የመጓጓዣ ወጪንም በእጅጉ ይቀንሳሉ። በሌላ በኩል ቤተሰቦች በጓሯቸው የሚያመርቱት ምርት የዕለት ተዕለት የምግብ ወጪያቸውን በመቀነስ የምግብ ዋስትናቸውን ያጠናክራል። ከቤተሰብ ፍጆታ በላይ የሚተርፈው ምርት ደግሞ ወደ ገበያ በመግባት የምግብ አቅርቦትን ያሳድጋል፤ በዚህም የዋጋ ንረትን በመቀነስ የገበያ መረጋጋትን ለማስፈን የጎላ አስተዋፅኦ ያደርጋል። የአረንጓዴ ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ የከተማ ግብርና የምግብ ምርትን ከማሳደግ ባለፈ፣ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር የከተማ ኢኮኖሚን የሚያነቃቃና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ መሠረትን የሚያጠናክር ዘርፍ ሆኗል። በአዲስ አበባን ጨምሮ በበርካታ የኢትዮጵያ ከተሞች በአትክልት፣ በፍራፍሬ፣ በዶሮ እርባታ፣ በወተት ሀብትና በንብ ማነብ የተሰማሩ በርካታ ወጣቶችና ሴቶች ቋሚ የገቢ ምንጭ እያገኙ ይገኛሉ። ይህም የከተማ ግብርና የቤተሰብ የምግብ ፍላጎትን ከማሟላት ባሻገር የሥራ አጥነትን ለመቀነስና የከተማ ኢኮኖሚን ለማጠናከር እያበረከተ ያለውን ጉልህ አስተዋፅኦ ያሳያል። አካባቢን ከመጠበቅ እስከ የከተሞችን ውበት የከተማ ግብርና የሥነ-ምህዳር ጠቀሜታውም ከፍተኛ ነው። ከቤት የሚወጡ ኦርጋኒክ ቆሻሻዎችን ወደ ተፈጥሯዊ ማዳበሪያ በመቀየር የአፈር ለምነትን ያሻሽላል፤ በተመሳሳይ ጊዜም የከተማ ጽዳትን ያጠናክራል። ከዚህ በተጨማሪ የአረንጓዴ ስፍራዎች መስፋፋት የከተሞችን የሙቀት መጠን በመቀነስ፣ የአየር ጥራትን በማሻሻልና ለነዋሪዎች ጤናማና ምቹ የኑሮ አካባቢ በመፍጠር ለከተማ ዘላቂነት የጎላ አስተዋፅኦ ያደርጋል። ማጠቃለያ የከተማ ግብርና የኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት የልማት አቅጣጫ መሆኑን በተግባር አረጋግጧል። የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ጀምሮ የኑሮ ውድነትን መቀነስ፣ የሥራ ፈጠራን ማስፋፋት፣ የከተሞችን ውበት ማጎልበትና የአረንጓዴ ኢኮኖሚን መገንባት ድረስ ያለው ሚና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎላ ነው። ስለሆነም ለከተማ ግብርና የሚስማሙ ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋት፣ ለወጣቶችና ለሴቶች የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍን ማጠናከር፣ የገበያ ትስስርን ማሻሻልና በከተማ ፕላን ውስጥ ለግብርና ተስማሚ ቦታዎችን በቋሚነት መመደብ ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው። ከተሞች የምግብ ፍጆታቸውን በራሳቸው የማምረት አቅም እያዳበሩ ሲሄዱ፤ የኢትዮጵያ ዘላቂ የምግብ ዋስትና፣ ጠንካራ አረንጓዴ ኢኮኖሚና ተወዳዳሪ የከተማ ልማት ስኬታማ ትልም ይበልጥ ይፋጠናል። ከደጃችን የሚጀምረው ምርት፤ ለሀገር ዕድገት የሚሆን ትልቅ አቅም ነው።
ትንታኔዎች
በተቃርኖ የተሞላው ሕገ ወጡ ሕወሓት የጥፋት ጉዞ
Jul 30, 2026 237
የሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የፖለቲካ ጉዞ በበርካታ መሠረታዊ ተቃርኖዎችና የፖለቲካ ስህተቶች የተሞላ ነው። ቡድኑ በትግል ጊዜም ይሁን ሀገርን በመምራት ባደረገው የፖለቲካ ተሳትፎ ታሪክ ይቅር የማይላቸው ስህተቶችን ፈጽሟል። ከሁሉም በላይ የትግራይን ሕዝብ ለዘመን ተሻጋሪ መከራና ስቃይ ዳርጓል። የወጣቶችን ተስፋ እና ሕልም አጨልሟል። የሕገ ወጡ ቡድን በተቃርኖ የተሞላ ጉዞ በጨረፍታ እንመልከት። ተቃርኖ አንድ፦ የሀገር ገዥነት እና የነጻ አውጪነት መንፈስ ሕገ ወጡ ሕወሓት ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ግንባር ፈጥሮ ሀገር በመራበት ዘመንም ጉዞው በተቃርኖ የተሞላ ነበር። በዚህ የሥልጣን ዘመኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ከአንድነት ይልቅ ልዩነትን፤ ከኅብረት ይልቅ መነጠልን ሥር እንዲሰድ አድርጓል። በስም ደረጃ ሕብረ ብሔራዊ የፌዴራል ሥርዓት እንደሚያራምድ ቢናገርም ለኢትዮጵያውያን የተለያየ የዳቦ ስም በመስጠት እርስ በእርስ እንዲጠራጠሩ በማድረግ የጥላቻ ፖለቲካን አንግሷል። የሕግ የበላይነት እና የሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት በአንዱ ቡድን ላይ የማይተገበር ሌላው ላይ ግን ተግባራዊ እንዲሆን አድርጓል። ከቡድኑ ጋር የጥቅም ትስስር ያላቸው ቡድኖች ለሕግ የማይገዙ፣ ከኮንትሮባንድ እስከ ዓለም አቀፍ ወንጀሎች ውስጥ የሚሳተፉ ነበሩ። ሌላው ጽንፈኛ፣ አክራሪ እና ተስፋፊ ተደርጎ በሽብር እየተወነጀለ በየማረሚያ ቤቱ እንዲንገላታ ተደርጓል። በጥቅሉ ሕገ-መንግሥት እና የፌዴራል ሥርዓትን ለራሱ በሚያመች መልኩ ሲጠቀምበት ቆይቷል። ከዚህም ባለፈ ሕገ ወጡ ቡድን ሀገርን እየመራ እንደ አንድ የክልል ነጻ አውጪ ድርጅት በብሔሮች መካከል ጥርጣሬና ልዩነት እንዲሰፋ የሚያደርጉ የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካዎችንም አንግሷል። ‘እኛ እና እነሱ’ የሚል ፖለቲካን ከማካሄድ ባለፈ ‘ልዩ ኃይል’ በሚል ወታደራዊ አደረጃጀት ፈጥሮ መንግሥት መስሎ ሀገርን የማፍረስ እና የማዳከም ተግባር ውስጥ ተሳትፏል። ተቃርኖ ሁለት፦ ሰሜን እዝን ባጠቃበት ጊዜ ሕገ ወጡ ቡድን ራሱ ያደራጀውን እና ሲያሞካሸው የቆየውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 2013 ዓ.ም. በማጥቃት የተቃርኖ ጉዞውን መቀጠሉን አረጋግጧል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን እዝ የትግራይ ሕዝብ ጋሻና መከታ፣ የችግር ጊዜ ደራሽ እና ከሻዕቢያ ተከላካይ ሆኖ ላቡንና ደሙን ገብሯል። ሕገ ወጡ ቡድን የሀገር ሉዓላዊነትና የሕገ-መንግሥት ጠባቂ ነኝ ሲል ቆይቶ፣ ለ20 ዓመታት በትግራይ ሕዝብ ደህንነት ጥበቃ ላይ የነበረውን እና የትግራይ ተወላጆችንም በሠራዊቱ ውስጥ ያቀፈውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት አጥቅቷል። ሴረኛው እና በተቃርኖ የተሞላው ቡድን የማይመርዝና የማይለውጠው መሆኑን ያረጋገጠበትን ድርጊት ፈጽሞ የሀገር ጋሻና መከታን አዋርዷል። ይህ ድርጊት በኢትዮጵያ ዘመናዊ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እጅግ አሳፋሪ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል። የተቃርኖው ውጤት ግን መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ባልተጠበቀ ሁኔታ አንድ ላይ አስተሳሰረ፤ ለሉዓላዊነትና ለግዛት አንድነት የአባቶቹን ታሪክ እንዲደግም ዕድል ፈጠረ። ተቃርኖ ሦስት፦ የሰላም ውል እና የውስጥ ክፍፍል ሕገ ወጡ ቡድን የሥልጣን ጥመኝነቱን ለማርካት ስፍር ቁጥር የሌላቸው የትግራይ ክልል ተስፋ የሆኑ ወጣቶችን በጦርነት ከማገደ በኋላ የሰላም ስምምነት ተፈረመ። በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ጦርነቱን ለማስቆም የተደረገ ወሳኝ እርምጃ ነበረ። ነገር ግን ከስምምነቱ በኋላ አሁንም ከስህተቱ የማይማረው ይህ ቡድን የተቃርኖ ጉዞውን መቀጠሉን ያረጋገጠበት ጥፋት ፈጸመ። ሕገ ወጡ ቡድን ስምምነቱን በይፋ ከተቀበለው በኋላ ስምምነቱን የሚጥሱ ድርጊቶችን መፈጸም ቀጠለ። መሣሪያ ለማስረከብ ተስማምቶ በስምምነቱ መሠረት መሄድ አቃተው፣ እንቅፋት ፈጠረ። በትጥቅ ውስጥ የቆዩ ወጣቶች ወደ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመለሱ ማድረግ ነበረበት፣ አላደረገም። ይልቅስ ለሌላ ጥፋት ውስጥ ለውስጥ መዘጋጀቱን ተያያዘው። ጊዜያዊ አስተዳደር ለመመስረት ተስማምቶ ወደ ተግባር ከተገባ በኋላ የጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮችን አልቀበልም በማለት ሕገ ወጥነቱን ቀጥሎ ለትግራይ ሕዝብ ሰላም እና እፎይታ የሰጠውን የሰላም ስምምነት አፈረሰ። ከጦርነቱ ማብቃት በኋላ ትኩረት መደረግ የነበረበት የወደሙ አካባቢዎችን መገንባት፣ የተፈናቀሉትን መመለስ እና ሰብዓዊ እርዳታ ማፋጠን ላይ መሆን ሲገባው፣ ሕገ ወጡ ቡድን ወደ ውጭ ይፋ በወጣ የሥልጣን ሽኩቻና የእርስ በእርስ ውንጀላ ውስጥ መዘፈቁ ለሕዝቡ ያለው ግድየለሽነት ማሳያ ሆኖ ተወሰደ። ለጥፋት ተልዕኮው ስኬት በፍጹም የዓላማም ይሁን የትግል አንድነት የለኝም ሲላቸው ከነበሩ የጥፋት ቡድኖች ጋር አበረ። ይህ ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመመሳጠር ሉዓላዊነትን ለማስደፈር እና ሀገር ለማፍረስ በሙሉ አቅሙ መንቀሳቀስ ጀመረ። ልብ ማለት የሚገባን ባህር በርን የሚያክል ጉዳይ እንደ ተራ ሸቀጥ ያየው ቡድን እንዴት ስለ ብሔራዊ ክብር እና ሉዓላዊነት ሊያስብ ይችላል? ሊሆን አይችልም። ተቃርኖ አራት፦ የሕገ ወጡ ቡድን የመጨረሻው የጥፋት ጉዞ ዓለምና የኢትዮጵያ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ሁኔታ በከፍተኛ ሁኔታ ቢቀየርም፣ ሕገ ወጡ ሕወሓት ግን አሁንም በ1960ዎቹ እና 70ዎቹ የትግል ስልት ተከተሏል። ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከሆኑት ባዕዳን ተልዕኮ ተቀብሎ ከሀገር ውስጥ ባንዳዎች ጋር አብሯል። ‘ጽምዶ’ ከተባለው የጥፋት ስብስብ ፊት አውራሪ በመሆን የለመደውን የተቃርኖ ጉዞ ለመቀጠል ተቅበዝብዟል። የወጣቱን የሥራ፣ የዲሞክራሲ፣ የኢኮኖሚና የዘመናዊነት ጥያቄ በትክክለኛ መንገድ ከመመለስ ይልቅ ወደ ሥልጣን ለመመለስ ለሚያደርገው የቀቢጸ ተስፋ ሙከራ እያደረገ ነው። ከምርጫ ቦርድ ጋር ያለው ሕጋዊ ሰውነት የማጣት አለመግባባት እና በሕጋዊ መንገድ ራሱን ለማደስ ፈቃደኛ አለመሆኑ ቡድኑን በሕግ ፊትም ሆነ በፖለቲካዊ ምህዳሩ ውስጥ ወደ መጨረሻው የመገለልና የውድቀት ምዕራፍ መርቶታል። ዛሬ ግን ትናንት አይደለም። ኢትዮጵያ ዘመኑን በዋጀ አመራር እየተመራች ትገኛለች። ዘመኑን ሙሉ የተቃርኖ ጉዞ ያደረገው ሕገ ወጡ ቡድን ወደ መጨረሻው የፖለቲካ ውድቀት እያመራ ነው። የሕገ ወጡ ቡድን የተቃርኖ ጉዞም የበቃል።
የኢትዮጵያዊያን ምክክር፤ የጋራ ነገን የሚያሻግር የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ድልድይ
Jul 22, 2026 699
በሚኪያስ ጎቡ መግቢያ፡- ሀገራት ከጦርነት በላይ የሚፈትናቸው ጠላት አለ፤ እርሱም በአንድ ሀገር ልጆች መካከል የሚፈጠረው የመተማመን መሰናክል ነው። መሣሪያ የፈጠረውን ጉዳት እንደገና መገንባት ይቻላል። የተሰበረ ልብና የጠፋ መተማመን ግን በጉልበት አይመለስም። ለዚህም ነው ብዙ ሀገራት ከግጭት በኋላ ወደ ምክክር የሚመለሱት። ብሔራዊ ምክክር የአንድ መንግሥት ፕሮጀክት ወይም የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአንድ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፈው የሰላም ውርስ ነው። የሚጋጩ ሃሳቦች በጠመንጃ ሳይሆን በቃል ሲገናኙ፣ የተለያዩ ትርክቶች በመደማመጥ ሲቀራረቡ፣ ልዩነቶችም የጥላቻ ምንጭ ሳይሆኑ የመግባባት መነሻ ሲሆኑ ነው እውነተኛ ሀገራዊ ምክክር የሚፈጸመው። የዓለም ተሞክሮ እንደሚያሳየው ብሔራዊ ምክክር አንድ ዓይነት ቀመር የለውም። እያንዳንዱ ሀገር በታሪኩ፣ በባህሉ፣ በፖለቲካዊ እውነታውና በማኅበራዊ መዋቅሩ መሰረት የራሱን መንገድ ይመርጣል። ነገር ግን የሁሉም ግብ አንድ ነው፤ ግጭትን በመግባባት፣ ጥላቻን በመተማመን፣ ፍርሃትን በተስፋ መተካት። በአውሮፓ ከኮሙኒዝም ውድቀት በኋላ፣ በአፍሪካ ከአምባገነናዊ አስተዳደሮች ሽግግር ወቅት፣ በደቡብ አሜሪካ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሂደቶችና በዓረቡ ዓለም ከፖለቲካ አብዮቶች በኋላ የተካሄዱ ምክክሮች አንድ ትልቅ ትምህርት ይሰጣሉ። ምክክር ሲታመን ሀገር ያድናል፤ ለፖለቲካ ጥቅም ሲውል ግን ቀውስን ያባብሳል። ይህ የኢትዮጵያም ትልቁ ፈተና ነው። ሀገራዊ ምክክር የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት ነው። የምንናገረው ቃል፣ የምንጽፈው ሐሳብ፣ የምናዳምጠው አቋምና የምንቀበለው ልዩነት የነገዋን ኢትዮጵያ ይቀርጻሉ። ምክክር የሚጀምረው በአዳራሽ ሳይሆን በሰዎች ልብ ውስጥ ነው፤ የሚሳካውም ከመናገር በላይ በመደማመጥ ሲቻል ነው። ስለዚህ የዛሬው ጥያቄ "ምክክር ይካሄድ ወይ?" የሚል አይደለም። "ምክክሩን ለሀገር የሚበጅ፣ ለትውልድ የሚተርፍ፣ ለታሪክ የሚያስከብር እንዴት እናድርገው?" የሚለው ነው። መልሱም በአካታችነት፣ በእውነት፣ በመከባበርና በሀገርን ከግል ጥቅም በላይ በማስቀደም ውስጥ ይገኛል። ምክክር፤ የሀገር መድኃኒት ወይስ የትውልድ ፈተና? ምክክር ለምን ያስፈልጋል?፡- ማንኛውም ሀገር የሚያድገው በሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ግንባታ ብቻ አይደለም። በሕዝቦቿ መካከል በሚኖረው መተማመን ጭምር እንጂ። መንገድ፣ ድልድይና ፋብሪካ መገንባት ይቻላል፤ ነገር ግን የተሰበረ ማኅበራዊ ትስስር ካልተጠገነ የልማቱ መሠረት ይናወጣል። ስለዚህ ብሔራዊ ምክክር የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን የሀገር የወደፊት ዕጣ ፋንታ የሚወሰንበት የጋራ አስተሳሰብ ሂደት ነው። የምክክሩ ዋና ዓላማ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር አይደለም። ይልቁንም ሁሉም ወገኖች የራሳቸውን እውነት እየገለጹ፣ የሌላውንም እውነት በማዳመጥ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ሂደት ነው። እውነተኛ የምክክር ድል የሚለካውም የማን ሃሳብ አሸነፈ ሳይሆን ለሀገር ምን ያህል ሰላምና መተማመን ፈጠረ በሚለው ነው። የዓለም ተሞክሮ የሚያስተምረን፡- የታሪክ ገጾች እንደሚያሳዩት ሀገራት የብሔራዊ ምክክርን መንገድ የመረጡት ሌሎች አማራጮች ሲያቅቷቸው ነው። አንዳንዶቹ የረዥም ጊዜ የፖለቲካ ቀውስ ነበራቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በሥልጣን ሽኩቻ ተከፋፍለው ሲራኮቶ የሰነባበቱ ናቸው። ነገር ግን የተሳካላቸው ሀገራት አንድ የጋራ መርህ ነበራቸው፤ የሀገርን ጥቅም ከፓርቲ፣ ከቡድንና ከግል ጥቅም በላይ አስቀድመዋል። ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ወደ ዴሞክራሲ የተሸጋገረችው በበቀል ሳይሆን በሰለጠነ ምክክር ነው። ፖላንድና ሀንጋሪ የፖለቲካ ሽግግራቸውን በየጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር አሳልፈዋል። ላይቤሪያና ሊባኖስ የጦርነት ቁስላቸውን ለማዳን የመደማመጥን መንገድ መርጠዋል። በተቃራኒው ግን ምክክርን ለፖለቲካ ሕጋዊነት ማግኛ፣ ለሥልጣን ማራዘሚያ ወይም ለውጭ ጫና ማስታገሻ ብቻ ያደረጉ ሀገራት የበለጠ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። ይህም አንድ ግልጽ ትምህርት ይሰጠናል፤ የምክክር ስኬት የሚወሰነው በመድረኩ ሳይሆን በተመካካሪዎች ቅንነት መሆኑን ያስረዳናል። ምክክር የሚጠይቀው ከባድ ኃላፊነት፡- ሀገራዊ ምክክር የኮሚሽን ወይም የመንግሥት ሥራ ብቻ አይደለም። የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነትን የሚጠይቅ የጋራ ነገ አሻጋሪ ድልድይና የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ነው። ፖለቲከኛው የሀገርን ጥቅም ማስቀደም፣ የሚዲያው እውነትን በሚዛናዊነት ማቅረብ፣ የሲቪክ ማኅበራት የተገለሉ ድምፆችን ማሰማት፣ የኃይማኖት ተቋማት ይቅርታና መቻቻልን ማስፋፋት፣ ወጣቱ ከጥላቻ ይልቅ ውይይትን መምረጥና ምሁራን በማስረጃ የተደገፈ ሃሳብ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ማንም ወገን የራሱን አቋም ብቻ ለማስገደድ ከሞከረ፣ ምክክሩ ወደ ክርክር ይቀየራል። ሁሉም ለመረዳት እንጂ ለማሸነፍ ካልመጡ ደግሞ የምክክሩ መንፈስ ይጠፋል። የሀገራዊ ምክክር ትልቁ ድል የሌላውን አቋም መለወጥ ሳይሆን፣ የሌላውን ህመም መረዳት ነው። ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር፤ ልዩነታቸው ምንድን ነው?፡- ብዙ ጊዜ ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር የሚሉት ቃላት በአንድ ትርጉም ይጠቀሳሉ። ነገር ግን በፖለቲካዊና በማኅበራዊ ሂደቶች እያንዳንዳቸው የተለየ ዓላማና ባህሪ አላቸው። ይህንን ልዩነት አለማወቅ ሀገራዊ ምክክርን ከመጀመሪያው ሊያዛባው ይችላል። ውይይት የሐሳብ ልውውጥ ነው። ሰዎች ስለ አንድ ጉዳይ አመለካከታቸውን ይገልጻሉ፣ ይደማመጣሉ። ሁልጊዜ ውሳኔ ላይ ላይደርስ ይችላል። ክርክር የሚያተኩረው የማን ሃሳብ ትክክል እንደሆነ ላይ ነው። የራስን አቋም በማስረጃ ለማስረዳት ይደረጋል፤ አንድ አሸናፊና አንድ ተሸናፊ ሊኖር ይችላል። ድርድር ደግሞ የጥቅም ግጭትን በመካከለኛ መፍትሔ ለመፍታት የሚደረግ ሂደት ነው። እያንዳንዱ ወገን ከአቋሙ በመቀነስ የጋራ መፍትሔ ለማግኘት ይሞክራል። ሀገራዊ ምክክር ግን ከእነዚህ ሁሉ የላቀ ሂደት ነው። ዓላማው ማንንም ማሸነፍ ወይም ማስሸነፍ ሳይሆን የሀገር የወደፊት አቅጣጫ ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። በምክክር ውስጥ የሚሸነፍ ሰው የለም፤ የሚያሸንፈው ሀገር ነው። የኢትዮጵያ ልዩ እውነታ፡- ኢትዮጵያ ሦስት ሺህ ዘመናትን የተሻገረ በሕብር ያሸበረቀ ታሪክ፣ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና ኃይማኖት ያላት ሀገር ናት። ይህ በሕብር ያሸበረቀ ልዩነት የኢትዮጵያ ጥንካሬ መሆን ሲገባው በተለያዩ ወቅቶች የፖለቲካ አለመግባባቶችና የታሪክ ትርክቶች የመከፋፈል መሣሪያ ሆነው ቆይተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ፈተናም ይህ ነው። ሁሉም የራሳቸውን ታሪክ ይዘው ወደ ጠረጴዛው ይመጣሉ፤ ነገር ግን ከጠረጴዛው የሚወጡት አንድ የጋራ የወደፊት ርዕይ ይዘው መሆን አለባቸው። ይህ ቀላል አይደለም። ስለዚህ ምክክሩ ከቃላት በላይ በተግባር የሚገለጥ ቅንነትን ይፈልጋል። የዋናው ምክክር ጉባኤ የህዝብ ወኪል ተመካካሪዎችም ሀገርን የማስቀደም ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ስኬታማ ምክክር የሚመሰረትባቸው አምስት ምሰሶዎች፡- ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን ቢያንስ አምስት መሠረታዊ ምሰሶዎች ሊኖሩት ይገባል። እነሱም መተማመን፣ አካታችነት፣ እውነት፣ ፍትሕና የጋራ ርዕይ ናቸው። ከሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበራሰብ የሕዝብ ወኪል 4 ሺ ተመካካሪ ኢትዮጵያዊያንም በሀገር ግንባታ ጉዳይ፣ የመንግስት አደረጃጃትና ስርአት ጉዳይ፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬድዋ ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና የመልካም አስተዳዳር ጉዳዮች፣ የሰላም ግንባታ ጉዳዮች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽ ማዕከል እየመከሩ ይገኛል። ሀገራዊ ምክክር ያለፈውን ለመቁጠር ሳይሆን፣ የወደፊቱን ለመገንባት የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው። የኢትዮጵያ መንገድም የልዩነት ግድግዳን የሚያፈርስ የትውልድ አደራና የብሔራዊ መግባባት ማሰሪያ ጥበብና ትልም ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፤ የተገኙ ዕድሎች፣ ዋና ፈተናዎች እና የወደፊት አቅጣጫ በታሪክ ጉዞዋ ውስጥ ኢትዮጵያ ብዙ የፈተና ዘመናትን አልፋለች። አንዳንዶቹ ፈተናዎች ከውጭ ጥቃት የመጡ ቢሆኑም፣ አብዛኞቹ ግን ከውስጣዊ አለመግባባቶች፣ ከተለያዩ የታሪክ ትርክቶች፣ ከፖለቲካ ፉክክርና ከመተማመን እጥረት የተፈጠሩ ናቸው። ስለዚህ የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት የዛሬን ችግር ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፣ የትውልድ ዕዳን ለማቃለል የተጀመረ ታሪካዊ ሂደት ነው። ይህ ሂደት ቀላል አይደለም። በርካታ ዓመታት የተከማቹ ቅሬታዎች፣ የተለያዩ እውነታዎች፣ የተቃራኒ ትርክቶችና የተለያዩ የፖለቲካ ፍላጎቶች በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መገናኘታቸው በራሱ ትልቅ ፈተና ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ ትልቁ ፈተና ልዩነትን ወደ መግባባት መቀየር ነው። ዕድሎች፤ ሊጠቀሙባቸው የሚገቡ ወሳኝ መስኮቶች፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ የምታነሳበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። የታሪክ አተረጓጎም፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የሥልጣን ክፍፍል፣ የሀብት አጠቃቀም፣ የፍትሕ ጉዳዮችና የአብሮነት ዕሴቶች በጦርነት ሳይሆን በሐሳብ የሚፈቱበት ዕድል ይፈጥራል። ከዚህም በላይ ምክክሩ የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር የሚያስችል ዕድል ነው። ለብዙ ዓመታት "አሸናፊና ተሸናፊ" በሚለው አስተሳሰብ የተመራውን ፖለቲካ ወደ "አብሮ ማሸነፍ" የሚሸጋግር ከሆነ እውነትም የኢትጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ ጠንካራ መሠረት ያገኛል። በሂደቱ ፊት የሚቆሙ ፈተናዎች፡- ማንኛውም ሀገራዊ ምክክር ከፍተኛ ተስፋ እንደሚፈጥር ሁሉ ከባድ ፈተናዎችንም ይዞ ይመጣል። የመጀመሪያው ፈተና የመተማመን እጥረት ነው። ለብዙ ዓመታት የተገነባ ጥርጣሬ በጥቂት ወራት አይጠፋም። ስለዚህ የምክክሩ ተዓማኒነት በእያንዳንዱ እርምጃ ሊገነባ ይገባል። ሁለተኛው ፈተና የተለያዩ የታሪክ ትርክቶች ናቸው። አንድ ክስተት በአንዱ ወገን የድል ታሪክ ሲሆን፣ በሌላው ወገን የመከራ ታሪክ ሊሆን ይችላል። ይህን ልዩነት በክብር መቀበል እንጂ መግፋት አይቻልም። በሌላ መልኩም የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ ስርጭት ነው። በዲጂታል ዘመን አንድ ያልተረጋገጠ መረጃ በጥቂት ደቂቃዎች ሺዎችን ሊደርስ ይችላል። ስለዚህ የሚዲያ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሚወስዱት ኃላፊነት ከመቼውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። የምሁራንና የመገናኛ ብዙኅን ሚና፡- በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ምሁራን ስሜትን ሳይሆን ማስረጃን ማቅረብ አለባቸው። የማኅበረሰብ ችግሮችን በሳይንሳዊ ጥናት መተንተን፣ ከሌሎች ሀገራት ልምድ መማርና አማራጭ መፍትሔዎችን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። መገናኛ ብዙኅንም በዚህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው። መገናኛ ብዙኅን ወሬን ከማባዛት ይልቅ እውነትን ማጣራት፣ ልዩነትን ከማባባስ ይልቅ መግባባትን ማጎልበት፣ ስሜትን ከማቀጣጠል ይልቅ እውነታን ማቅረብ አለበት። ምክክሩን የሚያጠናክር የመገናኛ አውታር ታሪክ ይሠራል፤ የሚያደናቅፍ ደግሞ በታሪክ ይጠየቃል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ቀን የሚጠናቀቅ ክስተት አይደለም። ምክክር በትውልድ የሚገነባ የፖለቲካ ባህል ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራውን ሊጨርስ ይችላል፤ ነገር ግን የመደማመጥ ባህል በሕዝብ ውስጥ ካልሰረጸ የምክክሩ እውነተኛ ዓላማ አይሳካም። የዛሬ ውሳኔ፤ የነገ ኢትዮጵያ፡- አንዳንድ የታሪክ ወቅቶች በየቀኑ አይመጡም። አንዳንድ ውሳኔዎችም የአንድ መንግሥት ዘመንን ብቻ ሳይሆን የትውልዶችን ዕጣ ፈንታ ይወስናሉ። ሀገራዊ ምክክር የእነዚህ ታሪካዊ ውሳኔዎች አንዱ ነው። ዛሬ በምንመርጠው የምክክር ባህል፣ በምንገነባው መተማመንና በምናሳየው የፖለቲካ ብስለት ላይ የነገዋን የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ተምሳሌት ኢትዮጵያ ያንፃል። ምክክር ሁሉንም ችግር በአንድ ጊዜ የሚፈታ አስማታዊ መፍትሔ አይደለም። ነገር ግን ጦርነትን ከውይይት፣ ጥላቻን ከመቻቻል፣ መከፋፈልን ከመተባበር የሚተካ ብልህ መንገድ ነው። የሚያደርገውም ልዩነቶችን ማጥፋት ሳይሆን ልዩነቶችን በአንድ ሀገር ጣሪያ ስር እንዴት እንደሚኖሩ የጋራ ሕግና ሥርዓት መፍጠር ነው። በእርግጥ ኢትዮጵያ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፋለች። የፖለቲካ አለመተማመን፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የፀጥታ ችግሮች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎችና የማኅበራዊ ስብራቶች በቀላሉ የሚያልፉ አይደሉም። ይሁን እንጂ እነዚህን ችግሮች በጥይት ከመፍታት ይልቅ በምክክር ለመፍታት መሞከር በራሱ የታሪክ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ ግን የአንድ ተቋም ብቻ አይደለም። የመንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኅን ተቋማት፣ የምሁራን፣ የወጣቶች፣ የሴቶችና የእያንዳንዱ ዜጋ የጋራ ኃላፊነት ነው። የሀገር ዕጣ ፋንታ ለአንድ ቡድን ብቻ የሚተው አይደለም፤ በጋራ የሚገነባ እንጂ። ከምክክር ወደ ባህል፡- ምክክሩ ተጠናቀቀ ማለት የሀገሪቱ ችግሮች ተፈቱ ማለት አይደለም። እውነተኛው ስኬት የሚለካው የመደማመጥ ባህል በማኅበረሰቡ ውስጥ ሲሰርጽ ነው። በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመገናኛ ብዙኅን፣ በፖለቲካ ተቋማትና በየቤቱ የመነጋገር ባህል ካልጠነከረ፣ ምክክሩ የሰነድ ውጤት ብቻ ሆኖ ይቀራል። የእውነተኛ ዴሞክራሲ መሠረት ተመሳሳይ አስተሳሰብ መኖር አይደለም፤ የተለያዩ አስተሳሰቦችን በሰላም የመቀበል ባህል መኖር ነው። ልዩነት የችግር ምንጭ ሳይሆን የጥንካሬ ምንጭ ሲሆን ነው አንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም የምታገኘው። የማጠቃለያ፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚያስፈልገው ብልህ አመራር ብቻ አይደለም፤ ታጋሽ ዜጎችንም ይፈልጋል። ሀገር የምትገነባው በግንብ ሳይሆን በመተማመን ነው። ሰላም የሚጸናውም በፍርሃት ሳይሆን በፍትሕ ነው። ዛሬ የምንመርጠው የምክክር መንገድ ነገ ለልጆቻችን የምንተወው ታሪክ ይሆናል። ስለዚህ በኢትዮጵያን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተደራጅተው የሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የዛሬ አጀንዳ ብቻ አይደሉም፤ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚቀርጽ የትውልድ አደራ እንጂ። የዋናው ምክክር ጉባኤ ተመካካሪ የሕዝብ ወኪሎችም ከግልና ቡድን ፍላጎት ይልቅ የቀጣዩን ትውልድና ሀገርን ማስቀደም ይጠበቅባቸውል። ምክክር የቃላት ልውውጥ ብቻ አይደለም፤ የተሰበረ መተማመንን የሚጠግን፣ የተከፋፈለ ማኅበረሰብን የሚያቀራርብ፣ የትውልድ ታሪክን በአዲስ ተስፋ የሚጽፍ ሀገራዊ ጥበብ ነው። የምንወስነው ዛሬ የምንወርሰውን ነገ ይበይናል። ምክክር የሀገር መድኅን ነው፤ ኢትዮጵያም እየመከረች ነው።
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 801
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 4772
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 11096
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 21125
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14157
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 19907
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ዓይነ ስውሩ የቧንቧ ሰራተኛ
Jul 31, 2026 610
ዋግ ኽምራ፤ሐምሌ 24/2018 (ኢዜአ) ፦"ዓይኖቼ ማየት ባይችሉም እጆቼ ተዓምር ይሰራሉ'' -ዓይነ ስውሩ የቧንቧ ሰራተኛ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ መለስ ጌታነህ የ62 ዓመት የእድሜ ባለጸጋ አዛውንት ናቸው፤ ከጊዜ በኋላ በመጣ ችግር የሁለት ዓይኖቻቸውን ብርሃን ያጡ ቢሆንም በአካባቢው ስመ ጥር የቧንቧ ሠራተኛ ናቸው። ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ ገና በወጣትነት ዕድሜያቸው የቧንቧ ሥራ ሙያን ቀስመው፣ በዋግ ኽምራ በሚገኙ ወረዳዎች በመንቀሳቀስ ለንጹሕ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት አሻራቸውን እያሳረፉ ያሉ ትጉህ ባለሙያ ናቸው። ቆላ በመውረድ፣ ደጋ በመውጣት፣ ተራራና ሸንተረሩን ሳይበግራቸው የውሃ መስመር በመዘርጋት ህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ እንዲደርሰው እያደረጉ ያሉ አዛውንት ናቸው። ለዚህም በተደጋጋሚ የምስጋና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በ1991 ዓ.ም የተፈራ ኃይሉ መታሰቢያ ጠቅላላ ሆስፒታል ሥራ ሲጀምር እሳቸው በቧንቧ ባለሙያነት በቋሚነት በመቀጠር፣ የውሃ መስመር በመዘርጋትና በመጠገን የሕክምና ክፍሎች ያልተቋረጠ ውሃ እንዲያገኙ ማድረግ ችለዋል። ይሁን እንጂ ከዕለታት በአንድ ቀን ሥራቸውን እያከናወኑ ባሉበት ወቅት ባላወቁት ምክንያት የሁለት ዓይኖቻቸውን ብርሃን ያጡበት አጋጣሚ በመከሰቱ ከቤት ለመዋል መገደዳቸውን ያወሳሉ። እንደ አቶ መለስ ገለጻ፡ “ዓይኔ ማየት ባለመቻሉ ራሴን ችዬ መንቀሳቀስ፣ እንደልቤ ሜትር ዘርግቼ ለክቼ መቁረጥና ገደል ላይ ተንጠልጥዬ የቧንቧ መስመር መዘርጋት አልችልም የሚል የተሸናፊነት ስሜት አድሮብኝ ተስፋ ቆርጬ ተቀምጬ ነበር” ይላሉ። በዚህ ወቅት ትጋታቸውንና ብርታታቸውን የሚያውቁ የሆስፒታሉ ዳይሬክተር የነበሩት ዶክተር ዓለማየሁ ትኩ፣ ወደ ሆስፒታሉ በመውሰድና በመምከር ሥራቸውን እንዲቀጥሉ እንዳገዟቸው አውስተዋል። ቀስ በቀስም አቶ መለስ ሜትር በመዘርጋትና መጋዝ በመጨበጥ ልኬታን አስተካክለው፣ መገጣጠሚያ ቦታዎችን በዳበሳ ለይተው የቧንቧ ሙያ ሥራቸውን እንደገና “ሀ” ብለው ማስቀጠላቸውን አመልክተዋል። ምንም እንኳን ከወረዳ ወረዳ ተንቀሳቅሶ መሥራት ባይችሉም፣ በግለሰብ ቤቶችና ድርጅቶች እየተንቀሳቀሱ የቧንቧ ጥገና ሥራቸውን በብቃት እያከናወኑ ያሉ ብቁ ባለሙያ ሆነው ቀጥለዋል። በሆስፒታሉም ከአገልግሎት ውጭ የነበሩ የውሃ መስመሮችን በመለየትና በአግባቡ በመጠገን፣ ለሐኪሞችና ለሕመምተኞች ወጥ የሆነ የንጹሕ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ “አንቱ” የተባሉ ባለሙያ ሆነዋል። አቶ መለስ በቧንቧ ሥራ ሳይገደቡ፣ በራዲዮ በሚቀርቡ የቴክኖሎጂ ፕሮግራሞች ባገኙት እውቀት ከአገልግሎት ውጭ የነበረውን የሆስፒታሉን የላውንድሪ (ልብስ ማጠቢያ) ማሽን በዳበሳ ጠግነው ወደ አገልግሎት በመመለስ ሆስፒታሉን ከወጪ ታድገዋል። “ብርሃን ከዓይን ብቻ ሳይሆን ከልብና ከመዳፋችንም ይገኛል” የሚሉት አቶ መለስ፣ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ምጣዶችን በመጠገንና ሌሎችንም የቴክኒክ ሥራዎች በመሥራት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን የሚያስተዳድሩ ጠንካራ የዕድሜ ባለፀጋ ናቸው። "የዓይን ብርሃኔን አጣሁ ብዬ አንድም ቀን አስቤ አላውቅም” የሚሉት አቶ መለስ፣ አሁን ላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ጣራ ላይ በመውጣት ጭምር ቧንቧ ጠግነው የሚወርዱ ባለሙያ ሆነዋል። “እኔ ሥራ ሳልሠራ ስውል ያመኛል” የሚሉት አቶ መለስ፣ ወጣቱ ሥራን ሳይንቅ ከሰራ ከትንሽ ነገር ተነስቶ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም ትልቅ ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚችል ምክራቸውን ለግሰዋል። ስለ ጉዳዩ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተፈራ ኃይሉ ጠቅላላ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምሩ ቢምረው እንዳሉት፡ ጋሽ መለስ የዓይን ብርሃናቸውን ቢያጡም በሙያቸው የትጋትና የ“ይቻላል” ተምሳሌት የሆኑ አዛውንት ናቸው። አዛውንቱ በሙያቸው የሆስፒታሉ የውሃ አቅርቦት እንዳይቋረጥ በማድረግ ለሕክምና ሥራ መቀላጠፍ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸው ለሌሎች ባለሙያዎች በታታሪነት፣ በሥራ ፍቅር እና በጥንካሬ አርዓያ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የአካባቢ ፀጋን በማወቅ የተገኘ ስኬት-የምህንድስና ምሩቁ ሞዴል አርሶአደር
Jul 30, 2026 257
የምህንድስና ምሩቁ ሞዴል አርሶአደር (በቀደሰ ተክሌ- ሚዛን አማን) እውቀት በቅድሚያ ራስን ለመለወጥ ከዚያም አልፎ ለሀገር ሲተርፍ ይበልጥ ትርጉም ይሰጣል። ማወቅ ከተማርነው ትምህርት የዘለለ መረዳት እንዲኖረን በማድረግ ለነገሮች ያለንን የእይታ አድማስ ያሰፋል። የ"ለምን?" ጥያቄዎችን በማንሳት በምላሹ መፍትሔ ለመስጠት ይሞክራል። በዚህም ረገድ ከተማሩበት ትምህርት ባሻገር ሌላ ዓለም እንዳለ በማሳየት በኩል ተምሳሌት የሚሆኑ አሉ። የዚህ ፅሁፍ ባለታሪክም ከምህንድስና ትምህርቱ ባሻገር ያለውን ፀጋ በእርጋታ ተመልክቶ ውጤታማ መሆን እንዴት እንደሚቻል ለሌሎች ምሳሌ የሆነ ወጣት ነው። ወጣቱ ኢንጂነር ይንገሥ ጌታቸው ይባላል። በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የአላሞ ቀበሌ ነዋሪ ነው። በአካባቢው ባከናወነው ውጤታማ የግብርና ሥራ ሞዴል አርሶ አደር የሚል ሌላ የማዕረግ ስያሜን አግኝቷል። ይንገስ አስተዳደጉ በግብርና ስራ ከተሰማሩ ቤተሰቦቹ የእርሻ ማሳ ጋር የተያያዘ ነው። ዕድሜው ለትምህርት ሲደርስ ከትምህርት ቤት መልስ ቤተሰቦቹን በግብርና ስራ ያግዛል። ይህም የእርሻ ሥራን በአግባቡ እንዲረዳ አድርጎታል። ቤተሰቦቹን የሚያግዝበት እጁ የሻከረ ጉልበቱ የበረታ ነበር። ከዚያ አለፍ ሲልም በትምህርቱ ጎበዝ ስለነበርም እስከ ዩኒቨርሲቲ ዘለቀ። በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምህንድስና ትምህርቱን አጠናቆ ተመረቀ። ወደ ቀዬው ሲመለስም ስራ ከመፈለግ ይልቅ ከልጅነቱ ጀምሮ በሚያውቀው የግብርና ስራ ላይ ለመሰማራት በመወሰን በአጭር ታጥቆ ወደ ስራ ገባ። ለዘመናት ውጤታማ ሳይሆን የቆየውን የእርሻ ስራ ወደ የተሻለ ደረጃ ላይ የማድረስ ራዕይን ሰንቆ እጁን ከጭቃ ጋር አገናኘ። ወጣት ይንገስ ወደ እርሻ ስራ ለምን እንደመጣ ሲናገር "ቤተሰቦቼ ዕድሜያቸውን ሙሉ በግብርና ሥራ ነው የቆዩት፤ ነገር ግን ለውጥ የሚባል ነገር የለም።" ይህ ቁጭት ነው እንግዲህ "ለምን?" የሚል የመብሰልሰል ጥያቄን ሊያጭርበት የቻለው። የዘልማድ አሰራር፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የግብዓት አጠቃቀም፣ በዕውቀት ያለመመራትና ሌሎች ምክንያቶች የእርሻ ስራውን ውጤታማ እንዳይሆን እንዳደረጉት ተገነዘበ። ለዚህም ክፍተትን ማየት፣ መንስኤ መለየት፣ ከዛም ለውጥን አልሞ ወደ ውጤት መቀየር መፍትሔ ሊሆን እንደሚችል ተረዳ። በትናንቱ መንገድ ባለመጓዝ የዘመነና ገበያው የሚፈልገውን ምርት ለማምረት ለራሱ ቃል ገባ፤ ከራሱ ጋር ተስማማ። ወጣቱ አካባቢው ለቅመማ ቅመም ምርት የተመቸ ፀጋን የታደለ መሆኑን ስለሚያውቅ ይህን ዕድል ለመጠቀም በማሰብ ውድ የሆኑ የቅመማ ቅመም ምርቶችን በማምረት ለገበያ ለማቅረብ ወጠነ። ወጥኖም አልቀረም ወደ ተግባር ለመቀየር ተንቀሳቀሰ። ይህን ጊዜ ነው የሕይወቱ አዲስ ምዕራፍ የተከፈተው። ከአላሞ ተነስቶ ወደ ቴፒ የግብርና ምርምር ማዕከል አቀና። ማዕከሉ በብሔራዊ ደረጃ በቅመማ ቅመም ላይ ትኩረት በማድረግ የምርምር ስራዎችን ይሰራል። የምርምር ማዕከሉ ከሚያወጣቸው ዝርያዎች መካከል ቫኒላ አንዱ ነው። ቫኒላ ደግሞ በዓለማችን ውዱ ቅመም ነው። ወጣቱ ይንገስም ፍላጎቱ ተሳክቶ ዝርያውን ከማዕከሉ በመውሰድ ማሳው ላይ ተክሎ መንከባከብ ጀመረ። የቫኒላ የአመራረት ሂደት ትዕግሥትን የሚጠይቅ ነው። በተለይ ፍሬ እንዲሰጥ እርስ በእርስ የማዳቀሉ ተግባር ጥብቅ ክትትልና ትጋትን የሚጠይቅ ነው። ሂደቱን ተሻግሮ ምርት እስከሚሰጥ ድረስ ወጣቱ ከባለሙያዎች ድጋፍን ከመጠየቅ ባሻገር ድረ-ገፅን በመጠቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ የቫኒላ አመራረት ያለበትን ደረጃ እስከ መከታተል የደረሱ ጥረቶችን ያደርጋል። በዚህም ብዙዎች ተስፋ የቆረጡበትን የቫኒላ ቅመም ምርት እርሱ በአግባቡ አልምቶ ውጤታማ እንዲሆን አድርጎታል። እነሆ አሁን ላይ ወጣቱ ካፒታሉን በማሳደግ በየዓመቱ ሚሊዮን ብሮችን ወደ ካዝናው የሚያስገባ ባለሃብት ሆኗል። በተጨማሪም ወጣቱ የቤተሰቡን ማሳ በአዲስ የቡና ዝርያ ለመሸፈን በሳይንስ የተደገፈ የማሳ ዝግጅት አድርጎ ቡና መትከል ጀመረ። እነሆ ዛሬ 5 ሄክታር በምርምር የተገኘ ምርጥ የቡና ዝርያ ለምቶ ፍሬ መስጠት ጀምሯል። ይህ የቡና ውጤታማነት ዝቅተኛ መልክዓ-ምድር ባላት የአላሞ ቀበሌ ከዚህ ቀደም የማይታሰብ አዲስ ብሥራት ነው። ከዚህ ቀደም የነበሩ የቡና ዝርያዎች ለቆላማ አካባቢ ተስማሚ ስላልነበሩ አርሶአደሮች ቡና አልምተው ብዙም ተጠቃሚ አይሆኑም ነበር። ወጣቱ የቴፒ ግብርና ምርምር ያወጣቸውን እንደ "K-1፣ K-2 እና I-3" በሚል ስያሜ የሚታወቁ የቡና ዝርያዎችን በመውሰድ በማሳው ላይ በመሞከር ውጤት አምጥቶለት ችግኞቹ በ9 ወር አብበው የምሥራች ፍሬ ሊሰጡ ችለዋል። ዝርያዎቹ በሙሉ አቅም ምርት ሲሰጡ በሄክታር ከ20 ኩንታል በላይ ምርት ይሰበሰብባቸዋል። ኢንጂነሩ ሞዴል አርሶ አደር በቫኒላ እና በቡና ልማት ላይ ብቻም ራሱን አልገታም። በአቮካዶ፣ በሙዝ፣ በአናናስ፣ በፓፓያና በሌሎች የፍራፍሬ ዓይነቶችን ጨምሮ በካካዎ እና በቁንዶ በርበሬ ቅመማ ቅመም ምርቶች ላይ በመሰማራትም ተጠቃሚ መሆን ችሏል። የካካዎን ምርት ለኢንዱስትሪ ግብዓት እንዲውል በማድረግ የውጭ ምንዛሬን የማዳን ዓላማን ይዞ ወደ ምርት መግባቱን ይናገራል። ካካዎ ቾኮሌት ለሚያመርት ፋብሪካ በግብዓትነቱ ተጠቃሽ ነው። ወጣት ይንገስ በተለያዩ ምርቶች ላይ ከመሰማራት ባሻገር የተሻሻሉ የዘር ችግኞችን እያባዛ ለአካባቢው አርሶ አደሮችም እያቀረበ ይገኛል። በዚህም በዓመት በሚሊዮን የሚቆጠር ገቢ በማግኘት ራሱን እና ቤተሰቡን የተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ አድርሷል። የሸካ ምድር ፍሬ ለመስጠት የምርት ዓይነት አይመርጥም። የሰጡትን ያበቅላል፤ ይህ ደግሞ በተፈጥሮ የተቸረ ጸጋ ነው። የወጣት ይንገሥ ማሳ አንድ ምርት ብቻን የማልማት ዕድልን ማን ይሰጠዋል። በጥምር የእርሻ ስነ-ዘዴ እርስ በእርስ ተመጋጋቢ የሆኑ የተለያዩ ምርቶች በአንድ ላይ ይመረታሉ። ለአብነትም አቮካዶ፣ ፓፓያና ሙዝ በአንድ ላይ ይመረታሉ። ይህም ውጤታማ የመሬት አጠቃቀም ሥርዓትን ፈጥሯል። ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ጥበቃ፣ ለጥላና የእንጨት ሥራ ውጤቶች ግብዓት የሚሆነው የግራቪላ ዛፍ ለቁንዶ በርበሬ ልማት መሠረት ሆኖ ያገለግላል። መንግሥት "ምግቤን ከጓሮዬ" በሚል ያስጀመረው ሀገራዊ ኢኒሼቲቭ ማሳያ ከሆኑ ማሳዎች ውስጥ የሚመደበው የወጣቱ ማሳ ከፋብሪካ ውጤቶች በቀር ይህ ጎደለ የሚባልለት አይደለም። ከወተት እስከ ማር፣ ከአትክልት እስከ አዝርዕት ሁሉም በመጠኑ ይመረታል። ውጤታማ የግብርና ሥራ መሬትን አርሶ ከዘር ጋር ከማገናኘት ያለፈ ትርጉም የሚፈልግ መሆኑን ከኢንጂነሩ ሞዴል አርሶ አደር ይንገሥ የሥራ ተሞክሮ መማር ይቻላል። በቴክኖሎጂ ዘመን ከቴክኖሎጂ ርቆ ማልማት ድካም ከማብዛት ውጭ ውጤቱ አርኪ አይደለም። የግብርና ምርቶችን በከፊል ማቀነባበር የሚችሉ ማሽኖችን በመትከል ምርቶቹን በጥራት ለዓለም አቀፍ ገበያ ለማቅረብ አቅዶ እየሠራ መሆኑን ጠቅሷል። ከወጣት ይንገሥ የሥራ ውጤታማነት በኋላ ብዙዎች የአካባቢው ወጣቶች ተነቃቅተዋል። ብዙ ዓመት ሰፊ ማሳ አልምተው ጥቂት ምርት ይሰበስቡ የነበሩ አርሶ አደሮችም ወደ ይንገሥ ማሳ ጎራ ብለው ተሞክሮ በመቅሰም ለትግበራው ወደ ማሳቸው አቅንተዋል። ተሞክሮውን ፈጥነው ወደ ውጤት ከቀየሩ ወጣቶች መካከል ወጣት ብርሃኑ ጌታቸው አንዱ ነው። እርሱም ዛሬ ሁለተኛ ዓመቱን የያዘ የ5 ሄክታር ቡና ማሳ ባለቤት ሆኗል። ቡናን ከመትከል በተጨማሪ ዘር በማፍሰስ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እንደሚያከናውን ገልጿል። አርሶ አደር ታደሰ እጅጉ፤ ላለፉት በርካታ ዓመታት በእርሻ ሥራ ቢቆዩም ውጤታማውን መንገድ ሳይከተሉ መቆየታቸውን ይናገራሉ። አሁን ላይ ወጣቶቹ ሠርተው ባመጡት ውጤት ተደስተው አሠራሩን በማሳቸው ለመተግበር መነሳሳታቸውን ገልጸዋል። ያላቸውን 10 ሄክታር የእርሻ ማሳ ከልጆቻቸው ጋር በማልማት በአዳዲስ የቡና፣ የቅመማ ቅመም እና የፍራፍሬ ልማት ለመሸፈን ማቀዳቸውን ጠቅሰዋል። አቶ ተስፋዬ ግዛው የየኪ ወረዳ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ጽሕፈት ቤት ባለሙያ ናቸው። በወጣት ይንገሥ ጌታቸው የተከናወነው ውጤታማ ሥራ የወረዳውን የግብርና ሥራ ያነቃቃ መሆኑን ተናግረዋል። በቡና ምርታማነት ላይ የታየው ተሞክሮ ወደ ሌሎች ቀበሌዎች እንዲስፋፋ እያደረግን ነው ብለዋል። በተለይ በጥምር እርሻ አመራረት ሥነ-ዘዴ የታየው የቅመማ ቅመም እና ፍራፍሬ ማሳ ውጤት በጠባብ ማሳ ብዙ የምርት መጠን መሰብሰብ የሚቻልበትን መንገድ በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። የኢንጂነሪንግ ምሩቁ ወጣት ተሞክሮ የአካባቢን ፀጋ ባለመመልከት በሥራ ፍለጋ ጊዜያቸውን ለሚያባክኑ ወጣቶች የሚያስተምረው ዘርፈ ብዙ ትምህርት አለ ብለዋል። የሰው ልጅ ሕይወት የሚቀየረው በሥራ ዓይነት ሳይሆን በጠንካራ የሥራ ባህል ነው። በእጅ ያለን ወርቅ እንደ መዳብ ቆጥሮ የሩቅ ከመሻት ይልቅ በአጠገብ ያለን ጸጋ አይቶ ወደ ውጤት መቀየር ነገን በተሻለ ደረጃ አሻግረን እንድናይ ያስችለናል። ለዚህ ደግሞ የኢንጂነሪንግ ምሩቁ ሞዴል አርሶ አደር ይንገሥ ጌታቸው ተግባር ሕያው ምስክር ነው። ሰላም!