ቀጥታ፡

በ8 የአጀንዳ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲመካከሩ የቆዩት የአጀንዳ ቡድኖች መግባባት ላይ ደረሱ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ከሁለት ቀናት በፊት በሰላም ግንባታ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በመንግስት አደረጃጀት እና የፖለቲካ ስርዓት ሲመካከሩ የነበሩ ቡድኖ መግባባት ላይ እንደደረሱ መገለፁ የሚታወስ ነው፡፡


 

በዛሬው ዕለትም የተቀሩት ማለትም በሀገር ግንባታ ፣በፌዴራል ከተሞች ጉዳይ፣ ተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነት እና ሰብዓዊ መብት፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተመካካሪዎች ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም