ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በከተማው በአዲሱ በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር ተገብቷል
Jul 10, 2026 77
ሀዋሳ፤ ሐምሌ3/2018(ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በአዲሱ በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር መገባቱን የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በከተማው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት እና የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች ለመመለስ ትኩረት መሰጠቱም ተመላክቷል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ መልኩ ማርቆስ ለኢዜአ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በከተማው ከ7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የዕቅዱን 102 ፐርሰንት ማሳካት ተችሏል፡፡ በ2019 ግብር ዘመን12 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር መገባቱን ገልፀው ከሐምሌ 1 ጀምሮ ገቢ የመሰብሰብ ሥራው መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት የገቢ አሰባሰብ ሥራው በቴክኖሎጂ መታገዙ፣ የባለሙያዎች አቅም መገንባቱና የገቢ ምንጮችን ማስፋት በመቻሉ ገቢን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል፡፡ በተያዘው የግብር ዘመንም የተጨማሪ እሴት ታክስ ገቢን የማሳደግ፣ ከቅጥር የሚገኝ ገቢን እና የአከራይ ተከራይ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ መልኩ አስረድተዋል፡፡ በከተማ አስተዳደሩ ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ ከጥሬ ገንዘብ ንክኪ ነፃ የሆነ የገቢ አሰባሰብ ሥርዐት በመዘርጋት በባንክ የክፍያ ማረጋገጫ ብቻ ገቢ እየተሰበሰበ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ ዓመት ጀምሮም የባንክ ክፍያን በማስቀረት በቴሌ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ እና ሌሎች ዘመናዊ የክፍያ አማራጮች ብቻ ገቢን ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ቅድመ ዝግጅቶች ተደርገው ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል፡፡ በከተማው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት እና የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች ለመመለስ ትኩረት መሰጠቱንም አመልክተዋል። ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ባለው የገቢ አሰባሰብ ሂደት ግብር ከፋዮች ግብራቸውን እየከፈሉ እንደሚገኙም አቶ መላኩ ጠቁመዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል በታቦር ክፍለ ከተማ በሸቀጣሸቀጥ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩት ወይዘሮ መስከረም አስፋው በየዓመቱ ግብራቸውን በወቅቱና በታማኝነት የመክፈል ልምድ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ከዜጎች የሚሰበሰበው ገቢ በከተማዋ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች እንደሚውል በመረዳታቸው በራሳቸው ተነሳሽነት ግብራቸውን በወቅቱ እንደሚከፍሉ ተናግረዋል፡፡ በግብር ሰብሳቢው አካል የሚሰጠው አገልግሎት በቴክኖሎጂ የታገዘና ከጊዜ ወደ ጊዜ ቅልጥፍናው እየጨመረ የመጣ በመሆኑ ያለ እንግልት ግብራቸውን በቀላሉ መክፈል እንደቻሉም ጠቁመዋል፡፡ በሀዋሳ መናኸሪያ ክፍለ ከተማ በእንግዳ ማረፊያ የአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ኢያሱ በገጄ ግብር ለሀገራችን የምንከፍለው የዜግነት ግዴታችን ነው ብለዋል፡፡ የከተማዋ የልማት ሥራ ጥቅሙ ለነዋሪው እንደሆነ ጠቅሰው ልማቱ እንዲፋጠን ግብራቸውን በአግባቡና በወቅቱ በመክፈል ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ቢሮው የአገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የተገልጋዩን እርካታ ማሳደግ ችሏል
Jul 10, 2026 97
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ በመደገፍና አዳዲስ አሰራሮችን በመዘርጋት የተገልጋዩን እርካታ ማሳደግ መቻሉን አስታወቀ። ቢሮው በ2018 በጀት ዓመት የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ያከናወናቸውን ተግባራት፣ የቢሮውን የለውጥ ጉዞና የተገኙ ስኬቶችን የሚያሳይ ኤግዚቢሽንም በዛሬው ዕለት በይፋ ከፍቷል። የቢሮው የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ ቢሮው የግብር ከፋዩን እንግልት ለመቀነስና ግልጽነትን ለመፍጠር በርካታ የሪፎርም ስራዎችን አከናውኗል። ወደ 24 የሚጠጉ አሰራሮች መዘርጋታቸውን ይህንንም በማሳተም ለተገልጋዩ ማህበረሰብ ተደራሽ መደረጉንና ከግብር ከፋዩ ሕብረተሰብ ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት መሰራቱን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት በቢሮው ስር ባሉ 17ቱም ቅርንጫፎች የሚገኙ ከሰባት ሺህ በላይ ሰራተኞችን መቆጣጠር የሚያስችል የቴክኖሎጂ አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም የአገልግሎት አሰጣጡ እንዴት እየተከናወነ እንደሚገኝ ዋና ቢሮ ሆኖ በቀጥታ መከታተል የሚያስችል የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋቱንም ጠቁመዋል፡፡ በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ የንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዘሃራ መሐመድ በበኩላቸው፤ ከቢሮው ጋር እየተደረገ ያለው የተቀናጀ አሰራር አዎንታዊ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ በተደረገው የጋራ ጥረትና ቅንጅታዊ አሰራር፣ ከነጋዴው ማህበረሰብ የተነሱ የተለያዩ ቅሬታዎችን በጋራ በመገምገም 620 ለሚሆኑ ነጋዴዎች ለገጠሟቸው ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና መግባባት የሰፈነባትን ሀገር ለትውልድ ለማሻገር ያስችላል
Jul 10, 2026 158
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ለቆዩ ያለመግባባቶች በሰለጠነ መንገድ በመመካከር ሀገራዊ መግባባት በመፍጠር፣ሰላምና ልማት በማስፈን ለትውልድ ለማሸጋገር የሚያስችል መሆኑን የሴቶች አደረጃጀት ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን፤ የዋናው ጉባኤ ተሳታፊ የሀገር ውስጥና የውጭ የሕዝብ ወኪሎችም አዲስ አበባ እየገቡ ይገኛሉ። በዋናው የምክክር ጉባኤም የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች (አዲስ አበባና ድሬዳዋ) ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣የተቋማት ግንባታ፣የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳይ፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም የሰላም ግንባታ የተሰኙ ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የሚመከርባቸው ይሆናል። የሴት አደረጃጀትና ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ችግሮቻችንን በምክክር ከመፍታት ይልቅ የኃይል አማራጭን በመከተል የፖለቲካ ፍላጎትን ለማስፈጸም የሚደረግ ጥረት አዋጭ አይደለም። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ለቆዩ ያለመግባባቶች በሰለጠነ ውይይት በመመካከር ሀገራዊ መግባባትን፣ሰላምና ልማት የሰፈነባትን ሀገር ለትውልድ ለማሸጋገር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ የሴቶችን ተሳትፎና አካታችነት የሚያረጋግጥና ሴቶች በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር ያላቸውን ፅኑ ፍላጎት ከግብ የሚያደርስ ስልጡን መንገድ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር ገነት ስዩም እንዳሉት፤ ሴቶች ሀገራዊ መግባባትን በመገንባት ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ሀገራዊ ጉዳዮችና ጥያቄዎች አሏቸው። በዚህም በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ ሂደት የነበረውን የሴቶች ንቁ ተሳትፎ በማሳደግ፣በዋናው ጉባኤም በወኪሎች አማካኝነት የሚሳተፉበት ዕድል መፈጠሩን አስረድተዋል። በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተካተቱ ዐበይት አጀንዳዎች የሴቶችንና የማህበረሰቡን የዘመናት ጥያቄ በስልጡን የውይይት መድረክ ትኩረት አግኝተው መፍትሔ እንደሚያገኙ እምነታቸውን ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት እናትዓለም እንዳለ በበኩላቸው፤ ለዘመናት በቆዩ አለመግባባቶች በሚከሰቱ ግጭቶች ሴቶች ግንባር ቀደም ተጠቂና የጉዳት ሰለባዎች ናቸው ብለዋል። በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰቢያና የተሳታፊ ልየታ ሂደትም ሴቶችን የሚመለከቱ የሕግና ፍትሕ፣ የሰብዓዊ መብት፣ የፍትሕ ተጠቃሚነትና የፖለቲካ ተሳትፎ አጀንዳዎች ተጠናቅረው መቅረባቸውን አስታውቀዋል። የሴቶች አጀንዳዎችም በዋናው የምክክር ጉባኤ በተካተቱ ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ውስጥ መካተታቸውን አስረድተዋል። የጉባኤው ተሳታፊ የሕዝብ ወኪሎችም ስልጡን ምክክርን በማስቀደም፣ጠንካራ ሀገረ መንግሥትና ሀገራዊ መግባባትን የሚያመጡ ምክረ ሃሳቦችን በታላቅ ኃላፊነት ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
በዞኑ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ ቀልጣፋና ግልጽነት የሰፈነበት አሰራርን በማረጋገጥ እያገዘ ነው
Jul 10, 2026 141
መቱ፤ ሐምሌ 3/2018 (ኢዜአ):- የኢሉአባቦር ዞን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ ቀልጣፋና ግልጽነት የሰፈነበት አሰራርን በማረጋገጥ የህብረተሰቡን እንግልት እየቀነሰ መሆኑ ተገለጸ። የኢሉአባቦር ዞን ያዮ ወረዳ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በዛሬው ዕለት ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል። የኢሉአባቦር ዞን አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ፤ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ማህበረሰቡን በታማኝነትና በቅንነት ለማገልገል ታልሞ የተቀረጸ ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በዞኑ ወደ ስራ የገቡ ማዕከላትም የህብረተሰቡን የአገልግሎት ተደራሽነት የሚያሰፋ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አሰራርን እያሰፈኑ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የተገልጋዩን ድካምና እንግልት ማስቀረት እያስቻለ መሆኑንም ገልጸዋል። በያዮ ወረዳ ስራ የጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 32 የስራ ክፍሎችን በአንድ ላይ ያካተተ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ በቀጣይም አሰራሩን በሁሉም የዞኑ ወረዳዎች ለማስፋፋት በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቀዋል። ከወረዳው ነዋሪዎች መካከል ቄስ ሳሙኤል ደምሴና ወይዘሮ ወርቄ ተፈራ፤ ማዕከሉ የተገልጋዩን መጉላላት የሚያስቀርና የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቱን የሚያሻሽል በመሆኑ ስራ መጀመሩ አስደስቷቸዋል። ብልሹ አሰራሮችን በመቀነስ ረገድ መንግስት እየወሰዳቸው የሚገኙት መሰል እርምጃዎች አበረታች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። ወይዘሮ ገላኔ ኮርሳና አቶ ጀማል ኢብራሂም በበኩላቸው፤ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ህዝቡን ከምልልስና ከተጨማሪ ወጪ የሚታደግ መሆኑን አንስተዋል። የመንግስት አገልግሎት ሰጪ መስሪያ ቤቶችም ከተለመደውና ለቅሬታ ከሚዳርጉ ብልሹ አሰራሮች በመላቀቅ፣ ማህበረሰቡን በታማኝነት የማገልገል ባህላቸውን ሊያሳድጉ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ተምሳሌቶቹ የቢሾፍቱ ከተማ የሌማት ትሩፋት ተጠቃሚዎች
Jul 10, 2026 160
የሌማት ትሩፋት ሀገራዊ ውጤት እና በመርሃ ግብሩ ህይወታቸውን ያሻሻሉ የቢሾፍቱ ነዋሪዎች ለብዙ ኢትዮጵያውያን ወተት፣ እንቁላል፣ ማርና ሥጋ በምግብ ገበታ የማይገኙ፣ ለረጅም ዓመታት የቅንጦት ያህል የሚታዩና በቂ ምርት ባለመኖሩም በገበያ ላይ በስፋት የማይገኙ ነበሩ። ይህንን እውነታ ለመቀየርና የዜጎችን የሥርዓተ ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመረው የሌማት ትሩፋት ሀገራዊ መርሃ ግብር ዛሬ ላይ ትልቅ ተስፋና ተጨባጭ ውጤት እያሳየ ይገኛል። ቀደም ሲል ትኩረት አጥቶ የነበረውን የእንስሳት ተዋጽኦ ልማት በቅንጅትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ ረገድ በአካባቢው ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል። በግብርና ሚኒስቴር መረጃ መሠረት መርሃ ግብሩ ከመጀመሩ በፊት የነበረው 7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ሊትር የወተት ምርት ዘንድሮ 15 ነጥብ 7 ቢሊዮን ሊትር መድረሱ፣ ቀደም ሲል በዓመት ይሰራጭ የነበረው የዶሮ ጫጩት ከ26 ሚሊዮን ወደ 184 ሚሊዮን ማደጉ እንዲሁም የእንቁላል ምርት ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ወደ 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ከፍ ማለቱ የዚሁ አገራዊ ስኬት ማሳያዎች ናቸው። ይህ የተጀመረው አበረታች ሂደት እንደ ወተት፣ ማር፣ ሥጋ፣ አሳ እና እንቁላል ያሉ ምርቶች የቅንጦት ሳይሆኑ የዜጎች የዕለት ተዕለት የሥርዓተ ምግብ አካል እንዲሆኑ በማስቻል ረገድም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በቢሾፍቱ ከተማና አካባቢዋ ለሚኖሩ በርካታ ዜጎች የአመጋገብ ሥርዓትን ከመቀየር ባለፈ፣ የኢኮኖሚ አቅማቸውን የለወጠ የሕይወት ጉዞን ፈጥሮላቸዋል። አቶ ከፈለኝ ጫላ ቀደም ሲል በመንግሥት ተቋም ተቀጥረው የሚሠሩ መደበኛ ሠራተኛ ነበሩ። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ላይ ዜጎች እንዲሳተፉ ጥሪ ሲቀርብ ግን የቀደማቸው አልነበረም። በተመቻቸላቸው የብድር አገልግሎት በመታገዝ በአንድ የወተት ላም ሥራቸውን ጀመሩ። ዛሬ ላይ ግን ታሪካቸው ሙሉ በሙሉ ተቀይሯል። የነበራቸውን ብቸኛ ላም ተንክባክበውና አርብተው በአሁኑ ወቅት የወተት ላሞቻቸውን ቁጥር 15 ማድረስ ችለዋል። "መንግሥት ያደረገልኝ ተከታታይ ድጋፍና ክትትል ለዚህ ውጤት እንድበቃ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቶልኛል" ይላሉ አቶ ከፈለኝ። የራሳቸውን ኑሮ ከመቀየር ባለፈ፣ የሚያመርቱትን ወተት ለአካባቢው ማኅበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን በማረጋጋት ረገድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። በተጨማሪም በመስኩ ለሌሎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል። ሌላኛው በዚሁ መርሃ ግብር ሕይወታቸው የተቀየረው ሥራ ፈጣሪ አቶ ጌቱ ብሩ ናቸው። እሳቸው ደግሞ በተቀናጀ የዶሮና የዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ላይ ነው የተሰማሩት። የሌማት ትሩፋት ያመጣላቸው በረከት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከመጥቀም አልፎ የንግድ አድማሳቸውን አስፍቶላቸዋል። ከልማቱ በሚያገኙት የምርት ውጤት የራሳቸውን ሆቴል መክፈት የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም አዲስ የሥራ ዕድል ፈጥረዋል። "ለሆቴላችን የምግብ ግብዓት የሚሆነውን ምርት የምናቀርበው ከራሳችን የዶሮና የዓሣ እርባታ ማዕከል ነው" የሚሉት አቶ ጌቱ፣ ዘርፉ ሰፊና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት የሚቻልበት መሆኑን ይመሰክራሉ። አቶ ጌቱ እቅዳቸው እዚህ ላይ ብቻ አያበቃም፤ በቀጣይ የሌማት ትሩፋት ምርቶችን እሴት ጨምረው ለከተሞች ከማቅረብ ባለፈ ወደ ውጭ ሀገር ለመላክና ለሀገር የውጭ ምንዛሬ የማስገኘት ውጥን አላቸው። ሌሎችም በዚህ ሥራ ላይ ቢሰማሩ ከራሳቸው አልፈው ሀገርንና ወገንን መለወጥ እንደሚችሉም ነው የጠቆሙት። በተመሳሳይ በዶሮ እርባታ ሥራ ላይ የተሰማሩት አቶ ደረጄ አበበ መርሃ ግብሩ ከፍተኛ ገቢ እንዲያገኙ እንዳስቻላቸው ይናገራሉ። የዶሮ እንቁላል ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለአካባቢው ማኅበረሰብ በስፋት በማቅረብ የኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም የበኩላቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)፥ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበትና የዜጎችን የምግብና ሥርዓተ ምግብ አቅም እያሳደገ የሚገኝ ኢኒሼቲቭ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ሀገራዊ ጥረት ለማሳካት የእንስሳት ሀብት ልማት ዘርፍ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ጠቅሰዋል። አክለውም፤ ኢኒሼቲቩ በቤተሰብ ደረጃ የዶሮ እርባታን ባህል እንዲሆን በማድረግ፣ በተለይም ሕፃናትና እናቶች የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ በማስቻል ረገድ መሠረታዊ ለውጥ እያመጣ መሆኑንና ምርቶችን በስፋት ለገበያ እንዲቀርቡ በማስቻል ረገድ ትርጉም ያለው ውጤት ማምጣቱን ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ሀገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና መግባባት የሰፈነባትን ሀገር ለትውልድ ለማሻገር ያስችላል
Jul 10, 2026 158
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ለቆዩ ያለመግባባቶች በሰለጠነ መንገድ በመመካከር ሀገራዊ መግባባት በመፍጠር፣ሰላምና ልማት በማስፈን ለትውልድ ለማሸጋገር የሚያስችል መሆኑን የሴቶች አደረጃጀት ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን፤ የዋናው ጉባኤ ተሳታፊ የሀገር ውስጥና የውጭ የሕዝብ ወኪሎችም አዲስ አበባ እየገቡ ይገኛሉ። በዋናው የምክክር ጉባኤም የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች (አዲስ አበባና ድሬዳዋ) ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣የተቋማት ግንባታ፣የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳይ፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም የሰላም ግንባታ የተሰኙ ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የሚመከርባቸው ይሆናል። የሴት አደረጃጀትና ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ችግሮቻችንን በምክክር ከመፍታት ይልቅ የኃይል አማራጭን በመከተል የፖለቲካ ፍላጎትን ለማስፈጸም የሚደረግ ጥረት አዋጭ አይደለም። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ለቆዩ ያለመግባባቶች በሰለጠነ ውይይት በመመካከር ሀገራዊ መግባባትን፣ሰላምና ልማት የሰፈነባትን ሀገር ለትውልድ ለማሸጋገር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ የሴቶችን ተሳትፎና አካታችነት የሚያረጋግጥና ሴቶች በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር ያላቸውን ፅኑ ፍላጎት ከግብ የሚያደርስ ስልጡን መንገድ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር ገነት ስዩም እንዳሉት፤ ሴቶች ሀገራዊ መግባባትን በመገንባት ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ሀገራዊ ጉዳዮችና ጥያቄዎች አሏቸው። በዚህም በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ ሂደት የነበረውን የሴቶች ንቁ ተሳትፎ በማሳደግ፣በዋናው ጉባኤም በወኪሎች አማካኝነት የሚሳተፉበት ዕድል መፈጠሩን አስረድተዋል። በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተካተቱ ዐበይት አጀንዳዎች የሴቶችንና የማህበረሰቡን የዘመናት ጥያቄ በስልጡን የውይይት መድረክ ትኩረት አግኝተው መፍትሔ እንደሚያገኙ እምነታቸውን ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት እናትዓለም እንዳለ በበኩላቸው፤ ለዘመናት በቆዩ አለመግባባቶች በሚከሰቱ ግጭቶች ሴቶች ግንባር ቀደም ተጠቂና የጉዳት ሰለባዎች ናቸው ብለዋል። በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰቢያና የተሳታፊ ልየታ ሂደትም ሴቶችን የሚመለከቱ የሕግና ፍትሕ፣ የሰብዓዊ መብት፣ የፍትሕ ተጠቃሚነትና የፖለቲካ ተሳትፎ አጀንዳዎች ተጠናቅረው መቅረባቸውን አስታውቀዋል። የሴቶች አጀንዳዎችም በዋናው የምክክር ጉባኤ በተካተቱ ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ውስጥ መካተታቸውን አስረድተዋል። የጉባኤው ተሳታፊ የሕዝብ ወኪሎችም ስልጡን ምክክርን በማስቀደም፣ጠንካራ ሀገረ መንግሥትና ሀገራዊ መግባባትን የሚያመጡ ምክረ ሃሳቦችን በታላቅ ኃላፊነት ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ለጫናዎች ያልተበገረ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ አከናውናለች- ምሁራን
Jul 10, 2026 588
ጅማ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ለጫናዎች ያልተበገረ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ ማከናወኗን የጅማና የመቱ ዩኒቨርሲቲዎች ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የውጭ ግንኙነትን በተመለከተ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ውስብስብ፣ አሻሚና ኢ-ተገማች በሆነ ዓለም ዲፕሎሚያዊ አካሄድ ፕራግማቲክ (ተለዋዋጭ) ሊሆን እንደሚገባ ማንሳታቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም አካሄዱ 3ቱ መ'ዎችን ማለትም መቋቋም፣ መጠቀም መግራት የሚባሉትን ተግባራዊ በማድረግ የዓለምን ተለዋዋጭ ባህሪ በመቋቋም የኢትዮጵያን የውሳኔ ሉዓላዊነት ማስጠበቅ መሆኑን አመልክተዋል። ይህንኑ በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ምሁራን እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ ለየትኛውም አካል ያልወገነ፣ ሚዛናዊ እና ጥንቃቄ የተሞላበት ዲፕሎማሲ መከተሏ ባለፉት አምስት ዓመታት ስኬቶችን እንድታስመዘግብ አድርጓታል። ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ለጫናዎች ያልተበገረ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ ማከናወኗንም ገልጸዋል። በመቱ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር ተገኝ ደምሴ፤ ያለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ጉዞ ቀላልና አልጋ በአልጋ እንዳልነበር ይናገራሉ። በተለይም ሀገሪቱ ከታሪካዊ ጠላቶቿ የሚሰነዘሩባትን ሴራዎች ጨምሮ በርካታ ጫናዎችን ብታስተናግድም፣ በሳል የሆነ የውሃ ዲፕሎማሲ ሥራ በመሥራት እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት መቻሏን ገልጸዋል። የዲፕሎማሲ ስራ ለአንድ ሀገር የእድገት ጉዞ እጅግ ወሳኝ በመሆኑ ዓለም አቀፍ ህጎችን ባከበረ መልኩ መንግስት የተከተለው የዲፕሎማሲ አቅጣጫ የውስጥ እና የውጭ ጫናዎችን በመቋቋም የሚፈለገው ስኬት እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል። በዚህም ኢትዮጵያ በራሷ ጥረትና ሀብት "ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ" በሚል መርህ በገጠሟት ፈተናዎች ጸንታ በመቆየት የግድብ ግንባታውን ማጠናቀቋ በቀጣናው ያላትን ተሰሚነት ማሳደግ መቻሉን አመልክተዋል። በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በያሉበት የሀገራቸው ዲፕሎማት ሆነው ኢትዮጵያ እንደ ባሕር በር ያሉ አስፈላጊ መብቷን በሴራ ማጣቷን በማስረዳት ምላሽ እስኪያገኝ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የህግ እና አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር ደሊል አህመድ በበኩላቸው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን ማስተናገዷና እንደ ብሪክስ ያሉ ስብስቦችን መቀላቀሏ በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተገኘ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሕግን ባከበረ መልኩ ፍትሐዊ አካሄድን መከተሏ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ማጠናቀቅ የመሰሉ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶችን ልታስመዘግብ መቻሏን ጠቅሰዋል። በኢኮኖሚው ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት፣ የጸጥታና የዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ በአንድም በሌላም መልኩ ለዲፕሎማሲው መጽናት ጠንካራ መሠረት እየሆኑ መምጣታቸውንም ምሁሩ አክለዋል። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዓለም አቀፍ ታዛቢ ተቋማት በተገኙበት ማካሄዷ የዚሁ የዲፕሎማሲ ስኬት አንዱ መገለጫ ነው ብለዋል። የባሕር በር ጉዳይ ኢትዮጵያ በታሪክም በሕግም የሚገባት ፍትሐዊ መብት መሆኑን ያብራሩት ምሁሩ፤ ይህንን ለማሳካት ሁለንተናዊ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶችን በማስቀጠል፣ ይበልጥ ውጤታማ ለመሆን ሁላችንም በጋራ ልንሰራ ይገባል ሲሉም ምሁራኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ለጠንካራ የሀገር ግንባታ እና ለዘላቂ አንድነት መሰረት እየጣለ ነው
Jul 10, 2026 470
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ለጠንካራ የሀገር ግንባታ እና ለዘላቂ አንድነት መሰረት እየጣለ መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶችና የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ባለፉት ዓመታት በአጀንዳ ማሰባሰብ እና በተሳታፊዎች ልየታ ላይ ሰፊ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። ኮሚሽኑ ከመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሂደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤም ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ እንዲሁም የሃይማኖት ጉዳዮች ከአጀንዳዎቹ መካከል ናቸው። የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም የሰላም ግንባታ ጉዳዮችም በዋናው ጉባኤ ምክክር የሚደረግባቸው አጀንዳዎች ናቸው። የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ይታሰብ ስዩም፤ ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ የሀገረ-መንግሥት ግንባታ ታሪክ ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል። ሆኖም በታሪክ ሂደት ላይ ያጋጠሙ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊና የኢኮኖሚ ቅራኔዎች ለተለያዩ ግጭቶችና አለመግባባቶች መንስኤ ሆነው ቆይተዋል ብለዋል። ኢትዮጵያውያን ለዘመናት አብረው የኖሩ፣ በችግር ጊዜ የሚደጋገፉና በመካከላቸው ያለው ማኅበራዊ ትስስር እጅግ የጠበቀ ሕዝቦች ናቸው ሲሉም ተናግረዋል። ይህንን ጠንካራ የእርስ በርስ ትስስር እና የዳበረ የባህል እሴት በመጠቀም፣ ማንኛውንም ችግሮች በጠረጴዛ ዙሪያ በመወያየት መፍታት እንደሚቻል ገልጸዋል። ለዚህም የተጀመረው የምክክር ሂደት ሀገራዊ መግባባትንና ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ አኳያ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑንም ጠቁመዋል። የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መሐመድ ኡስማን (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ለዘመናት የዘለቁና ውይይት እንዲሁም ምክክር የሚፈልጉ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን አንስተዋል። ልዩነቶችን በሐሳብ የበላይነትና በጋራ መግባባት ማስተናገድ መቻሉ ለሀገር አንድነትና ሉዓላዊነት ያለው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው ብለዋል። ይህ የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሀገር ግንባታ ሂደት ዘላቂነት እንዲኖረውና ጤናማ የትውልድ ቅብብሎሽ እንዲኖር ለማድረግ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አሁን የሚደረጉ ምክክሮች የትውልድ ቅብብሎሹ ስኬታማ እንዲሆንና መጪው ትውልድ የውይይትና የሰላም ባህልን እንዲያጎለብት አስተዋጽኦ ይኖረዋል ነው ያሉት። የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስማማው ዘገየ (ዶ/ር) ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለሀገር አንድነትና ለጠንካራ የሀገር ግንባታ መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ምክክሩ አሁን ያሉ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ ለቀጣዩ ትውልድ የተረጋጋችና የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ ያስችላል ብለዋል። የትምህርት ተቋማት በምክክሩ ሂደት ንቁ ተሳትፎ ማድረጋቸውን ገልጸው፣ ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አክለዋል።
የምክክር ኮሚሽኑ የለያቸው አጀንዳዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ናቸው
Jul 10, 2026 477
ደሴ ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የለያቸው ስምንቱ የምክክር አጀንዳዎች ለዘላቂ ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ናቸው ሲሉ ምሁራን ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ሃሳብ ለማካተት ጥረት የተደረገበት መሆኑን አንስተው እድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ማለታቸው ይታወሳል። በወሎ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ተባባሪ ፕሮፌሰር ቴዎድሮስ ካሴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የምክክር ኮሚሽኑ የለያቸው የምክክር አጀንዳዎች ስር የሰደዱ ችግሮችን በመለየት መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችሉ ናቸው። ኮሚሽኑ ለዘመናት የዘለቁ ልዩነቶችንና አለመግባባቶችን በምክክር በመፍታት፣ ለዘላቂ ሰላምና ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት መጎልበት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ለረጅም ጊዜ ሲንከባለሉ የቆዩ ልዩነቶችን በሰለጠነ አግባብ በመፍታት ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገትና ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረትን የሚጥል መሆኑን ተናግረዋል። የምክክሩ ሂደት አሳታፊ ከመሆኑም በላይ የተለዩት የምክክር አጀንዳዎችም ችግሮችን የሚፈቱና ሰላምን ለማምጣት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። በምክክር የማይፈታ ችግር የለም ያሉት ምሁሩ፤ ሁሉም በየደረጃው ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የምክክሩን ቀሪ ሂደት ውጤታማ ማድረግ፣ የጋራ ትርክት ለመገንባትና ሀገርን ለመታደግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው የታሪክ መምህርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር ጋሻው መሐመድ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት የሚያስችል መሆኑን እስካሁን ከመጣበት ሂደት መረዳት ተችሏል ብለዋል። መገፋፋትን፣ የፖለቲካ መጠላለፍንና መገለልን በማስቀረት ችግሮችን በውይይት መፍታት እንደሚቻል ለትውልድም ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። የተለዩት የምክክር አጀንዳዎችም ወቅታዊና ለችግሮች መፍትሔ ለመፈለግ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። አጀንዳዎቹ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ ለአደረጃጀትና ቅርጽ፣ ለሰላም ግንባታና ሌሎች ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችሉ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የምክክር ጉባኤ ስምንት ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው።
የተፈጠረው አሳታፊና አካታች የፖለቲካ ሥርዓት በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል
Jul 10, 2026 525
ወልቂጤ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ የተፈጠረው አሳታፊና አካታች የፖለቲካ ስርዓት በሃገር ሰላምና ልማት ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችል እድል መፍጠሩን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 30ኛ መደበኛ ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ባሳለፍነው ማክሰኞ ዕለት መካሄዱ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዲሞክራሲ ግንባታና የፖለቲካ ተሳትፎን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በወቅቱም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ብልጽግና ፓርቲ 85 በመቶ መቀመጫ ላይ ብቻ በመወዳደር ቀሪውን ለተፎካካሪ ፓርቲዎች በመተው፣ የዲሞክራሲ ቀናዒነት የታየበት ምርጫ ማካሄዱን ገልጸዋል። በጉዳዩ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ በሀገሪቱ የተፈጠረው አሳታፊና አካታች የፖለቲካ ሥርዓት በሀገር ሰላምና ልማት ላይ በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። የክልሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢዜማ ፓርቲ ተወካይ አቶ ደምስ ገብሬ እንዳሉት፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ የመረጠበትና በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት ነው። ፓርቲያቸው ኢዜማም በምርጫው በመሳተፍ ለክልልና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎችን ማግኘቱን ጠቅሰው፤ ባለፉት ዓመታትም በብልጽግና መንግሥት የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የነበረውን ሚና በተገቢው መንገድ መወጣቱን ገልጸዋል። መንግሥት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቶችን አቅም በማዳበር የአጋዥነት ሚና እንዲኖራቸው ማድረጉ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ደምስ፤ በቀጣይም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ ሊተገበሩ በታሰቡ ጉዳዮች ዙሪያ የሰጡት ዝርዝር ማብራሪያ አሳታፊና አካታች የፖለቲካ ሥርዓት ለመዘርጋቱ አመላካች መሆኑን ያነሱት ደግሞ የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባልና የጎጎት ፓርቲ ተወካይ አብዱላዚዝ ሙሰማ (ዶ/ር) ናቸው። ሀገር የሚገነባው በሁሉም ኢትዮጵያውያን አስተዋፅኦና ርብርብ በመሆኑ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ በትብብርና በጤናማ ፉክክር መሥራት ይገባናል ብለዋል። የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢና የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ናሰር ሐሰን በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግሥት የዲሞክራሲ ሥርዓትን ለማጎልበት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ፤ የአገልግሎት ዘመናቸውን ካጠናቀቁ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ጋር አብሮ ለመሥራት ያሳዩት ፍላጎት አካታችና አሳታፊ የፖለቲካ ሥርዓት ለመኖሩ ማረጋገጫ ነው ሲሉም አመልክተዋል።
መንግሥት የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ ነው
Jul 9, 2026 1664
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ መሆኑን አስተያየታቸውን የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግሥት የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ለመገንባት ሁልጊዜም ቢሆን የሰላም በር ክፍት ማድረጉን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይል ከምንጊዜውም በላይ በአስተማማኝ ቁመና ላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊትም በላቀ ቴክኖሎጂና በሰው ኃይል በጽኑ መሠረት መገንባቱን አብራርተዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል እንደሌለም ነው አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም፤ የኢትዮጵያን ሰላም፣ ልማትና ዕድገት ለማደናቀፍ የሚጥሩ የውስጥ ኃይሎች ፍላጎት ፈጽሞ አይሳካም ብለዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ትንኮሳ የሚፈጽም አንዳች ኃይል ቢኖር እንኳን ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ደኅንነት ለማስከበር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ገዛኸኝ ደበበ፤ ቅድመ አያቶች በከፈሉት ውድ መስዋዕትነት ትውልዱ ሉዓላዊ ነፃነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን እንዲረከብ ማስቻሉን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅትም ዜጎች በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ክብር ላይ ሊቃጣ የሚችልን አንዳች ትንኮሳ ለመቀልበስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመሸከም ኢትዮጵያን ለማወክ የሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ ኃይሎችም፣ ውይይትና ምክክርን በማስቀደም ለሀገር ሉዓላዊ ክብር በጋራ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ፀሐይ አሰፋ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአጭር ዓመታት ውስጥ በሁሉም ዘርፍ አስደማሚ የልማት ውጤት እያስመዘገበች እንደሚገኝ ገልጸዋል። በጫካ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበል፣ ውይይትና ምክክርን አስቀድመው ለኢትዮጵያ ዕድገት መፋጠን በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። በሁሉም ዘርፍ የሚመዘገበው የኢትዮጵያ የልማት ውጤት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በጸሎት ዮሐንስ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ልማት በማስቀጠል፣ ለሀገር ሉዓላዊ ደኅንነት ከመንግሥት ጋር በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል። ቅድመ አያቶች በዓድዋ፤ የአሁኑ ትውልድ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬት ያደረጉት በሕብር የታተመ አንድነትም፣ ማንኛውንም የውጭ ትንኮሳና ጫና መቀልበስ እንደሚቻል ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ሌላኛዋ የመዲናዋ ነዋሪ ፀሐይ ተፈራ በበኩላቸው፤ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሚሰጠው ተደጋጋሚ ዕድል የሀገር ልማትና ዕድገትን ለማስቀጠል የሚመነጭ ቁርጠኛ አቋም መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም የሀገርን ሰላምና ዕድገት ለማስቀጠል ከመንግሥት ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ በትብብር መስራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት።
ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው
Jul 9, 2026 1463
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የተከማቹ ችግሮችን የሚፈታ በመሆኑ ዕድሉን መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በምክክሩ ሂደት ከታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል ጀምሮ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ አጀንዳ የተለየበት መሆኑን ጠቁመው፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን ጠቃሚ ሒደት ነው ብለዋል። የምክክሩ ዋና ዓላማ ባለፉት ዘመናት ለቅራኔ ምንጭ የሆኑና የተከማቹ ችግሮችን በጋራ መክሮ መልክ ማስያዝ እንደሆነ ጠቅሰው፣ አዲስ ማኅበራዊ ውል የሚፈጸምበት መሆኑንም አመልክተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያና የሀገራዊ ምክክር ሂደትን አስመልክቶ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች፤ ምክክር የችግሮችን መንስኤና መፍትሔ በትክክል ለመለየት የሚያስችል ቀዳሚ መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩንና ታሪካዊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መካሄድ፣ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስታውቀዋል። ይህ ወሳኝ ምዕራፍ ስኬታማ እንዲሆንም ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በንቃትና በኃላፊነት ስሜት ሊሳተፍ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ሰላማዊት ጌትነት እንደተናገሩት፤ ምክክር በሀገር ውስጥ ያሉ ችግሮችንና መፍትሔዎቻቸውን በግልጽ ለመለየት ያስችላል። በኢትዮጵያ የሚካሄደው ምክክር ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የተረጋጋች ሀገርን ለመገንባት ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑን አንስተዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ያሬድ ደምሌ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አለመግባባቶችን በመፍታት የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠናከረ ሀገር መገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ ጦርነትና ግጭት ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጡ መታወቅ እንዳለበት የገለጹት አቶ ያሬድ፤ ምክክሩ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥና የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ወሳኝ ሚና እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል። አቶ ኃይሌ ባህረ፤ ሃገራዊ ምክክሩ የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ መሣሪያ መሆኑን በመጥቀስ በሀገሪቱ ያሉ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግሮ ለመፍታት የሚያስችል ምቹ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ወይዘሮ ወሰንየለሽ ገብሩ በበኩላቸው፤ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የምክክር ባህልን ማሳደግ አማራጭ የሌለው ተግባር በመሆኑ የሚደረገው ምክክር ለዘላቂ ሰላም ሆነ ልማትን ለማስቀጠል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ስታከናውነው የቆየችው የሀገራዊ ምክክር ሂደት አሁን ላይ የመጨረሻና ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተመካካሪዎች አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡
መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር መስፋት የሰጠው ትኩረት ለሀገር ዕድገት በትብብር መሥራትን የሚያጠናክር ነው
Jul 9, 2026 1340
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር መስፋት የሰጠው ትኩረት ለሀገር ዕድገት በትብብር መሥራትን የሚያጠናክር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በገዥው ፓርቲ ብልፅግና እና በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ የመሥራትና ሚዛኑን የጠበቀ የፉክክርና የትብብር ምህዳር ተገንብቷል። በዚህም የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ተመድበው እየሠሩ ሲሆን ይህም አካታች የፖለቲካ ጉዞን ከመክፈቱ በላይ ሀገርን በጋራ የማገልገል የትብብር አቅምን አሳድጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በሰጡት ማብራሪያ፥ ብልፅግና ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ 85 በመቶ በሆኑ ወንበሮች ላይ ብቻ በመወዳደር፣ በቀሪው 15 በመቶ ወንበር ላይ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻቸውን እንዲወዳደሩ ዕድል መስጠቱን ተናግረዋል። በምርጫው በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሳተፋቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር ግንባታ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፥ መንግሥት ለአሳታፊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚያደርገው ጥረት፤ ለሀገራዊ መግባባት፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመሥራትና ለአካታች ፖለቲካ ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም ጠቁመዋል። ወይዘሮ መታሰቢያ ጠብቀው፤ 15 በመቶ ወንበሮች ላይ ሳይወዳደር ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻ ክፍት ማድረጉ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ይሁነኝ ብሎ እየሠራ መሆኑን ያስመሰከረ ነው ብለዋል። ሁሉንም ያሳተፈ ሥርዓት መገንባት፣ መንግሥት የጀመራቸውን የልማት ሥራዎች በትብብር ለማፋጠንና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ ለመሥራት አቅም መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ሴቶች ወደ አመራርነት የመምጣት አጋጣሚያቸው እጅግ ውስን የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በሁሉም ዘርፎች እኩል ተሳታፊ መሆን መቻላቸው ሌላው የአካታችነት መገለጫ መሆኑን ጠቁመዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ዳዊት ይርባ በበኩላቸው፤ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማጠናከር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል። የመንግሥት ቁርጠኝነት በሐሳብ ልዕልና ላይ የተመሠረተ ፉክክርና ትብብርን በማስፋት ለዘላቂ ሰላምና ልማት መሠረት እንደሚሆን ጠቁመዋል። ወይዘሮ ውበት ደጉ በበኩላቸው፤ አሳታፊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዜጎች ሐሳባቸውን በነፃነት በመግለጽ ለሀገራቸው ልማትና ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ዕድል እንደሚፈጥር አብራርተዋል። አቶ ሺመልስ ከተማም መንግሥት በተባበረ መንፈስ ለመሥራትና ለአካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያሳየው ቁርጠኝነት በሀገሪቱ የፖለቲካ ጉዞ ትልቅ ተስፋን የሚዘራ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በእያንዳንዱ ዜጋ ዘንድ መደማመጥ፣ መግባባትና መተሳሰብን እንደሚፈጥር እምነታቸውን ገልጸዋል። አሳታፊ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታው ዘላቂ እንዲሆን የውይይት ባህል ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ ዶክተር ፍቅሩ ደስታ ናቸው። መንግሥት ሁሉንም ያሳተፈ እና በውይይት ላይ የተመሠረተ አካሄድ ለመከተል ቁርጠኛ መሆኑ ዘላቂ ሰላምና መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው አስገንዝበዋል።
ፖለቲካ
ሀገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና መግባባት የሰፈነባትን ሀገር ለትውልድ ለማሻገር ያስችላል
Jul 10, 2026 158
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ለቆዩ ያለመግባባቶች በሰለጠነ መንገድ በመመካከር ሀገራዊ መግባባት በመፍጠር፣ሰላምና ልማት በማስፈን ለትውልድ ለማሸጋገር የሚያስችል መሆኑን የሴቶች አደረጃጀት ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን፤ የዋናው ጉባኤ ተሳታፊ የሀገር ውስጥና የውጭ የሕዝብ ወኪሎችም አዲስ አበባ እየገቡ ይገኛሉ። በዋናው የምክክር ጉባኤም የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች (አዲስ አበባና ድሬዳዋ) ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣የተቋማት ግንባታ፣የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳይ፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም የሰላም ግንባታ የተሰኙ ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የሚመከርባቸው ይሆናል። የሴት አደረጃጀትና ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ችግሮቻችንን በምክክር ከመፍታት ይልቅ የኃይል አማራጭን በመከተል የፖለቲካ ፍላጎትን ለማስፈጸም የሚደረግ ጥረት አዋጭ አይደለም። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ለቆዩ ያለመግባባቶች በሰለጠነ ውይይት በመመካከር ሀገራዊ መግባባትን፣ሰላምና ልማት የሰፈነባትን ሀገር ለትውልድ ለማሸጋገር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ የሴቶችን ተሳትፎና አካታችነት የሚያረጋግጥና ሴቶች በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር ያላቸውን ፅኑ ፍላጎት ከግብ የሚያደርስ ስልጡን መንገድ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር ገነት ስዩም እንዳሉት፤ ሴቶች ሀገራዊ መግባባትን በመገንባት ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ሀገራዊ ጉዳዮችና ጥያቄዎች አሏቸው። በዚህም በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ ሂደት የነበረውን የሴቶች ንቁ ተሳትፎ በማሳደግ፣በዋናው ጉባኤም በወኪሎች አማካኝነት የሚሳተፉበት ዕድል መፈጠሩን አስረድተዋል። በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የተካተቱ ዐበይት አጀንዳዎች የሴቶችንና የማህበረሰቡን የዘመናት ጥያቄ በስልጡን የውይይት መድረክ ትኩረት አግኝተው መፍትሔ እንደሚያገኙ እምነታቸውን ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት እናትዓለም እንዳለ በበኩላቸው፤ ለዘመናት በቆዩ አለመግባባቶች በሚከሰቱ ግጭቶች ሴቶች ግንባር ቀደም ተጠቂና የጉዳት ሰለባዎች ናቸው ብለዋል። በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰቢያና የተሳታፊ ልየታ ሂደትም ሴቶችን የሚመለከቱ የሕግና ፍትሕ፣ የሰብዓዊ መብት፣ የፍትሕ ተጠቃሚነትና የፖለቲካ ተሳትፎ አጀንዳዎች ተጠናቅረው መቅረባቸውን አስታውቀዋል። የሴቶች አጀንዳዎችም በዋናው የምክክር ጉባኤ በተካተቱ ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ውስጥ መካተታቸውን አስረድተዋል። የጉባኤው ተሳታፊ የሕዝብ ወኪሎችም ስልጡን ምክክርን በማስቀደም፣ጠንካራ ሀገረ መንግሥትና ሀገራዊ መግባባትን የሚያመጡ ምክረ ሃሳቦችን በታላቅ ኃላፊነት ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ለጫናዎች ያልተበገረ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ አከናውናለች- ምሁራን
Jul 10, 2026 588
ጅማ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ለጫናዎች ያልተበገረ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ ማከናወኗን የጅማና የመቱ ዩኒቨርሲቲዎች ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የውጭ ግንኙነትን በተመለከተ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ውስብስብ፣ አሻሚና ኢ-ተገማች በሆነ ዓለም ዲፕሎሚያዊ አካሄድ ፕራግማቲክ (ተለዋዋጭ) ሊሆን እንደሚገባ ማንሳታቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም አካሄዱ 3ቱ መ'ዎችን ማለትም መቋቋም፣ መጠቀም መግራት የሚባሉትን ተግባራዊ በማድረግ የዓለምን ተለዋዋጭ ባህሪ በመቋቋም የኢትዮጵያን የውሳኔ ሉዓላዊነት ማስጠበቅ መሆኑን አመልክተዋል። ይህንኑ በማስመልከት ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ምሁራን እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ ለየትኛውም አካል ያልወገነ፣ ሚዛናዊ እና ጥንቃቄ የተሞላበት ዲፕሎማሲ መከተሏ ባለፉት አምስት ዓመታት ስኬቶችን እንድታስመዘግብ አድርጓታል። ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ለጫናዎች ያልተበገረ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ ማከናወኗንም ገልጸዋል። በመቱ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር ተገኝ ደምሴ፤ ያለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ጉዞ ቀላልና አልጋ በአልጋ እንዳልነበር ይናገራሉ። በተለይም ሀገሪቱ ከታሪካዊ ጠላቶቿ የሚሰነዘሩባትን ሴራዎች ጨምሮ በርካታ ጫናዎችን ብታስተናግድም፣ በሳል የሆነ የውሃ ዲፕሎማሲ ሥራ በመሥራት እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት መቻሏን ገልጸዋል። የዲፕሎማሲ ስራ ለአንድ ሀገር የእድገት ጉዞ እጅግ ወሳኝ በመሆኑ ዓለም አቀፍ ህጎችን ባከበረ መልኩ መንግስት የተከተለው የዲፕሎማሲ አቅጣጫ የውስጥ እና የውጭ ጫናዎችን በመቋቋም የሚፈለገው ስኬት እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል። በዚህም ኢትዮጵያ በራሷ ጥረትና ሀብት "ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ" በሚል መርህ በገጠሟት ፈተናዎች ጸንታ በመቆየት የግድብ ግንባታውን ማጠናቀቋ በቀጣናው ያላትን ተሰሚነት ማሳደግ መቻሉን አመልክተዋል። በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በያሉበት የሀገራቸው ዲፕሎማት ሆነው ኢትዮጵያ እንደ ባሕር በር ያሉ አስፈላጊ መብቷን በሴራ ማጣቷን በማስረዳት ምላሽ እስኪያገኝ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የህግ እና አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር ደሊል አህመድ በበኩላቸው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን ማስተናገዷና እንደ ብሪክስ ያሉ ስብስቦችን መቀላቀሏ በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተገኘ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሕግን ባከበረ መልኩ ፍትሐዊ አካሄድን መከተሏ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ማጠናቀቅ የመሰሉ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶችን ልታስመዘግብ መቻሏን ጠቅሰዋል። በኢኮኖሚው ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት፣ የጸጥታና የዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ በአንድም በሌላም መልኩ ለዲፕሎማሲው መጽናት ጠንካራ መሠረት እየሆኑ መምጣታቸውንም ምሁሩ አክለዋል። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዓለም አቀፍ ታዛቢ ተቋማት በተገኙበት ማካሄዷ የዚሁ የዲፕሎማሲ ስኬት አንዱ መገለጫ ነው ብለዋል። የባሕር በር ጉዳይ ኢትዮጵያ በታሪክም በሕግም የሚገባት ፍትሐዊ መብት መሆኑን ያብራሩት ምሁሩ፤ ይህንን ለማሳካት ሁለንተናዊ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶችን በማስቀጠል፣ ይበልጥ ውጤታማ ለመሆን ሁላችንም በጋራ ልንሰራ ይገባል ሲሉም ምሁራኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ለጠንካራ የሀገር ግንባታ እና ለዘላቂ አንድነት መሰረት እየጣለ ነው
Jul 10, 2026 470
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ለጠንካራ የሀገር ግንባታ እና ለዘላቂ አንድነት መሰረት እየጣለ መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶችና የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ባለፉት ዓመታት በአጀንዳ ማሰባሰብ እና በተሳታፊዎች ልየታ ላይ ሰፊ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። ኮሚሽኑ ከመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሂደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤም ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ እንዲሁም የሃይማኖት ጉዳዮች ከአጀንዳዎቹ መካከል ናቸው። የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም የሰላም ግንባታ ጉዳዮችም በዋናው ጉባኤ ምክክር የሚደረግባቸው አጀንዳዎች ናቸው። የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ይታሰብ ስዩም፤ ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ የሀገረ-መንግሥት ግንባታ ታሪክ ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል። ሆኖም በታሪክ ሂደት ላይ ያጋጠሙ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊና የኢኮኖሚ ቅራኔዎች ለተለያዩ ግጭቶችና አለመግባባቶች መንስኤ ሆነው ቆይተዋል ብለዋል። ኢትዮጵያውያን ለዘመናት አብረው የኖሩ፣ በችግር ጊዜ የሚደጋገፉና በመካከላቸው ያለው ማኅበራዊ ትስስር እጅግ የጠበቀ ሕዝቦች ናቸው ሲሉም ተናግረዋል። ይህንን ጠንካራ የእርስ በርስ ትስስር እና የዳበረ የባህል እሴት በመጠቀም፣ ማንኛውንም ችግሮች በጠረጴዛ ዙሪያ በመወያየት መፍታት እንደሚቻል ገልጸዋል። ለዚህም የተጀመረው የምክክር ሂደት ሀገራዊ መግባባትንና ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ አኳያ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑንም ጠቁመዋል። የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መሐመድ ኡስማን (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ለዘመናት የዘለቁና ውይይት እንዲሁም ምክክር የሚፈልጉ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን አንስተዋል። ልዩነቶችን በሐሳብ የበላይነትና በጋራ መግባባት ማስተናገድ መቻሉ ለሀገር አንድነትና ሉዓላዊነት ያለው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው ብለዋል። ይህ የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሀገር ግንባታ ሂደት ዘላቂነት እንዲኖረውና ጤናማ የትውልድ ቅብብሎሽ እንዲኖር ለማድረግ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አሁን የሚደረጉ ምክክሮች የትውልድ ቅብብሎሹ ስኬታማ እንዲሆንና መጪው ትውልድ የውይይትና የሰላም ባህልን እንዲያጎለብት አስተዋጽኦ ይኖረዋል ነው ያሉት። የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስማማው ዘገየ (ዶ/ር) ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለሀገር አንድነትና ለጠንካራ የሀገር ግንባታ መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ምክክሩ አሁን ያሉ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ ለቀጣዩ ትውልድ የተረጋጋችና የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ ያስችላል ብለዋል። የትምህርት ተቋማት በምክክሩ ሂደት ንቁ ተሳትፎ ማድረጋቸውን ገልጸው፣ ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አክለዋል።
የምክክር ኮሚሽኑ የለያቸው አጀንዳዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ናቸው
Jul 10, 2026 477
ደሴ ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የለያቸው ስምንቱ የምክክር አጀንዳዎች ለዘላቂ ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ናቸው ሲሉ ምሁራን ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ሃሳብ ለማካተት ጥረት የተደረገበት መሆኑን አንስተው እድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ማለታቸው ይታወሳል። በወሎ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ተባባሪ ፕሮፌሰር ቴዎድሮስ ካሴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የምክክር ኮሚሽኑ የለያቸው የምክክር አጀንዳዎች ስር የሰደዱ ችግሮችን በመለየት መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችሉ ናቸው። ኮሚሽኑ ለዘመናት የዘለቁ ልዩነቶችንና አለመግባባቶችን በምክክር በመፍታት፣ ለዘላቂ ሰላምና ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት መጎልበት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ለረጅም ጊዜ ሲንከባለሉ የቆዩ ልዩነቶችን በሰለጠነ አግባብ በመፍታት ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገትና ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረትን የሚጥል መሆኑን ተናግረዋል። የምክክሩ ሂደት አሳታፊ ከመሆኑም በላይ የተለዩት የምክክር አጀንዳዎችም ችግሮችን የሚፈቱና ሰላምን ለማምጣት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። በምክክር የማይፈታ ችግር የለም ያሉት ምሁሩ፤ ሁሉም በየደረጃው ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የምክክሩን ቀሪ ሂደት ውጤታማ ማድረግ፣ የጋራ ትርክት ለመገንባትና ሀገርን ለመታደግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው የታሪክ መምህርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር ጋሻው መሐመድ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት የሚያስችል መሆኑን እስካሁን ከመጣበት ሂደት መረዳት ተችሏል ብለዋል። መገፋፋትን፣ የፖለቲካ መጠላለፍንና መገለልን በማስቀረት ችግሮችን በውይይት መፍታት እንደሚቻል ለትውልድም ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። የተለዩት የምክክር አጀንዳዎችም ወቅታዊና ለችግሮች መፍትሔ ለመፈለግ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። አጀንዳዎቹ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ ለአደረጃጀትና ቅርጽ፣ ለሰላም ግንባታና ሌሎች ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችሉ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የምክክር ጉባኤ ስምንት ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው።
የተፈጠረው አሳታፊና አካታች የፖለቲካ ሥርዓት በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል
Jul 10, 2026 525
ወልቂጤ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ የተፈጠረው አሳታፊና አካታች የፖለቲካ ስርዓት በሃገር ሰላምና ልማት ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችል እድል መፍጠሩን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 30ኛ መደበኛ ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ባሳለፍነው ማክሰኞ ዕለት መካሄዱ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዲሞክራሲ ግንባታና የፖለቲካ ተሳትፎን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በወቅቱም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ብልጽግና ፓርቲ 85 በመቶ መቀመጫ ላይ ብቻ በመወዳደር ቀሪውን ለተፎካካሪ ፓርቲዎች በመተው፣ የዲሞክራሲ ቀናዒነት የታየበት ምርጫ ማካሄዱን ገልጸዋል። በጉዳዩ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ በሀገሪቱ የተፈጠረው አሳታፊና አካታች የፖለቲካ ሥርዓት በሀገር ሰላምና ልማት ላይ በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። የክልሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢዜማ ፓርቲ ተወካይ አቶ ደምስ ገብሬ እንዳሉት፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ የመረጠበትና በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት ነው። ፓርቲያቸው ኢዜማም በምርጫው በመሳተፍ ለክልልና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎችን ማግኘቱን ጠቅሰው፤ ባለፉት ዓመታትም በብልጽግና መንግሥት የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የነበረውን ሚና በተገቢው መንገድ መወጣቱን ገልጸዋል። መንግሥት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቶችን አቅም በማዳበር የአጋዥነት ሚና እንዲኖራቸው ማድረጉ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ደምስ፤ በቀጣይም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ ሊተገበሩ በታሰቡ ጉዳዮች ዙሪያ የሰጡት ዝርዝር ማብራሪያ አሳታፊና አካታች የፖለቲካ ሥርዓት ለመዘርጋቱ አመላካች መሆኑን ያነሱት ደግሞ የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባልና የጎጎት ፓርቲ ተወካይ አብዱላዚዝ ሙሰማ (ዶ/ር) ናቸው። ሀገር የሚገነባው በሁሉም ኢትዮጵያውያን አስተዋፅኦና ርብርብ በመሆኑ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ በትብብርና በጤናማ ፉክክር መሥራት ይገባናል ብለዋል። የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢና የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ናሰር ሐሰን በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግሥት የዲሞክራሲ ሥርዓትን ለማጎልበት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ፤ የአገልግሎት ዘመናቸውን ካጠናቀቁ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ጋር አብሮ ለመሥራት ያሳዩት ፍላጎት አካታችና አሳታፊ የፖለቲካ ሥርዓት ለመኖሩ ማረጋገጫ ነው ሲሉም አመልክተዋል።
መንግሥት የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ ነው
Jul 9, 2026 1664
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሰላም በሩን ክፍት ማድረጉ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ካለው ቁርጠኛ አቋም የሚመነጭ መሆኑን አስተያየታቸውን የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም መንግሥት የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ለመገንባት ሁልጊዜም ቢሆን የሰላም በር ክፍት ማድረጉን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይል ከምንጊዜውም በላይ በአስተማማኝ ቁመና ላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊትም በላቀ ቴክኖሎጂና በሰው ኃይል በጽኑ መሠረት መገንባቱን አብራርተዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የሚሆን አንዳች ኃይል እንደሌለም ነው አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም፤ የኢትዮጵያን ሰላም፣ ልማትና ዕድገት ለማደናቀፍ የሚጥሩ የውስጥ ኃይሎች ፍላጎት ፈጽሞ አይሳካም ብለዋል። በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ትንኮሳ የሚፈጽም አንዳች ኃይል ቢኖር እንኳን ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ደኅንነት ለማስከበር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ገዛኸኝ ደበበ፤ ቅድመ አያቶች በከፈሉት ውድ መስዋዕትነት ትውልዱ ሉዓላዊ ነፃነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን እንዲረከብ ማስቻሉን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅትም ዜጎች በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ክብር ላይ ሊቃጣ የሚችልን አንዳች ትንኮሳ ለመቀልበስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመሸከም ኢትዮጵያን ለማወክ የሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ ኃይሎችም፣ ውይይትና ምክክርን በማስቀደም ለሀገር ሉዓላዊ ክብር በጋራ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ፀሐይ አሰፋ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአጭር ዓመታት ውስጥ በሁሉም ዘርፍ አስደማሚ የልማት ውጤት እያስመዘገበች እንደሚገኝ ገልጸዋል። በጫካ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበል፣ ውይይትና ምክክርን አስቀድመው ለኢትዮጵያ ዕድገት መፋጠን በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። በሁሉም ዘርፍ የሚመዘገበው የኢትዮጵያ የልማት ውጤት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በጸሎት ዮሐንስ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም ከመንግሥት ጋር በመተባበር የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ልማት በማስቀጠል፣ ለሀገር ሉዓላዊ ደኅንነት ከመንግሥት ጋር በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል። ቅድመ አያቶች በዓድዋ፤ የአሁኑ ትውልድ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬት ያደረጉት በሕብር የታተመ አንድነትም፣ ማንኛውንም የውጭ ትንኮሳና ጫና መቀልበስ እንደሚቻል ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ሌላኛዋ የመዲናዋ ነዋሪ ፀሐይ ተፈራ በበኩላቸው፤ መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሚሰጠው ተደጋጋሚ ዕድል የሀገር ልማትና ዕድገትን ለማስቀጠል የሚመነጭ ቁርጠኛ አቋም መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም የሀገርን ሰላምና ዕድገት ለማስቀጠል ከመንግሥት ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ በትብብር መስራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት።
ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው
Jul 9, 2026 1463
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ አንድነቷ የተጠናከረና ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የተከማቹ ችግሮችን የሚፈታ በመሆኑ ዕድሉን መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በምክክሩ ሂደት ከታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል ጀምሮ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ አጀንዳ የተለየበት መሆኑን ጠቁመው፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን ጠቃሚ ሒደት ነው ብለዋል። የምክክሩ ዋና ዓላማ ባለፉት ዘመናት ለቅራኔ ምንጭ የሆኑና የተከማቹ ችግሮችን በጋራ መክሮ መልክ ማስያዝ እንደሆነ ጠቅሰው፣ አዲስ ማኅበራዊ ውል የሚፈጸምበት መሆኑንም አመልክተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያና የሀገራዊ ምክክር ሂደትን አስመልክቶ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች፤ ምክክር የችግሮችን መንስኤና መፍትሔ በትክክል ለመለየት የሚያስችል ቀዳሚ መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩንና ታሪካዊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መካሄድ፣ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስታውቀዋል። ይህ ወሳኝ ምዕራፍ ስኬታማ እንዲሆንም ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በንቃትና በኃላፊነት ስሜት ሊሳተፍ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ሰላማዊት ጌትነት እንደተናገሩት፤ ምክክር በሀገር ውስጥ ያሉ ችግሮችንና መፍትሔዎቻቸውን በግልጽ ለመለየት ያስችላል። በኢትዮጵያ የሚካሄደው ምክክር ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት የተረጋጋች ሀገርን ለመገንባት ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑን አንስተዋል። ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ያሬድ ደምሌ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ አለመግባባቶችን በመፍታት የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠናከረ ሀገር መገንባት ያስችላል ብለዋል፡፡ ጦርነትና ግጭት ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጡ መታወቅ እንዳለበት የገለጹት አቶ ያሬድ፤ ምክክሩ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥና የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ወሳኝ ሚና እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል። አቶ ኃይሌ ባህረ፤ ሃገራዊ ምክክሩ የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ መሣሪያ መሆኑን በመጥቀስ በሀገሪቱ ያሉ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግሮ ለመፍታት የሚያስችል ምቹ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። ወይዘሮ ወሰንየለሽ ገብሩ በበኩላቸው፤ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የምክክር ባህልን ማሳደግ አማራጭ የሌለው ተግባር በመሆኑ የሚደረገው ምክክር ለዘላቂ ሰላም ሆነ ልማትን ለማስቀጠል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ስታከናውነው የቆየችው የሀገራዊ ምክክር ሂደት አሁን ላይ የመጨረሻና ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተመካካሪዎች አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡
መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር መስፋት የሰጠው ትኩረት ለሀገር ዕድገት በትብብር መሥራትን የሚያጠናክር ነው
Jul 9, 2026 1340
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር መስፋት የሰጠው ትኩረት ለሀገር ዕድገት በትብብር መሥራትን የሚያጠናክር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በገዥው ፓርቲ ብልፅግና እና በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ የመሥራትና ሚዛኑን የጠበቀ የፉክክርና የትብብር ምህዳር ተገንብቷል። በዚህም የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ተመድበው እየሠሩ ሲሆን ይህም አካታች የፖለቲካ ጉዞን ከመክፈቱ በላይ ሀገርን በጋራ የማገልገል የትብብር አቅምን አሳድጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በሰጡት ማብራሪያ፥ ብልፅግና ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ 85 በመቶ በሆኑ ወንበሮች ላይ ብቻ በመወዳደር፣ በቀሪው 15 በመቶ ወንበር ላይ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻቸውን እንዲወዳደሩ ዕድል መስጠቱን ተናግረዋል። በምርጫው በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሳተፋቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መንግሥት ለአካታች የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምህዳር ግንባታ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፥ መንግሥት ለአሳታፊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚያደርገው ጥረት፤ ለሀገራዊ መግባባት፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመሥራትና ለአካታች ፖለቲካ ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም ጠቁመዋል። ወይዘሮ መታሰቢያ ጠብቀው፤ 15 በመቶ ወንበሮች ላይ ሳይወዳደር ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻ ክፍት ማድረጉ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ይሁነኝ ብሎ እየሠራ መሆኑን ያስመሰከረ ነው ብለዋል። ሁሉንም ያሳተፈ ሥርዓት መገንባት፣ መንግሥት የጀመራቸውን የልማት ሥራዎች በትብብር ለማፋጠንና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ ለመሥራት አቅም መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ሴቶች ወደ አመራርነት የመምጣት አጋጣሚያቸው እጅግ ውስን የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በሁሉም ዘርፎች እኩል ተሳታፊ መሆን መቻላቸው ሌላው የአካታችነት መገለጫ መሆኑን ጠቁመዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ዳዊት ይርባ በበኩላቸው፤ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማጠናከር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል። የመንግሥት ቁርጠኝነት በሐሳብ ልዕልና ላይ የተመሠረተ ፉክክርና ትብብርን በማስፋት ለዘላቂ ሰላምና ልማት መሠረት እንደሚሆን ጠቁመዋል። ወይዘሮ ውበት ደጉ በበኩላቸው፤ አሳታፊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዜጎች ሐሳባቸውን በነፃነት በመግለጽ ለሀገራቸው ልማትና ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ዕድል እንደሚፈጥር አብራርተዋል። አቶ ሺመልስ ከተማም መንግሥት በተባበረ መንፈስ ለመሥራትና ለአካታች የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያሳየው ቁርጠኝነት በሀገሪቱ የፖለቲካ ጉዞ ትልቅ ተስፋን የሚዘራ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በእያንዳንዱ ዜጋ ዘንድ መደማመጥ፣ መግባባትና መተሳሰብን እንደሚፈጥር እምነታቸውን ገልጸዋል። አሳታፊ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታው ዘላቂ እንዲሆን የውይይት ባህል ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ ዶክተር ፍቅሩ ደስታ ናቸው። መንግሥት ሁሉንም ያሳተፈ እና በውይይት ላይ የተመሠረተ አካሄድ ለመከተል ቁርጠኛ መሆኑ ዘላቂ ሰላምና መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው አስገንዝበዋል።
ማህበራዊ
የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ሥራዎች የእሳት አደጋና የጎርፍ ተጋላጭነትን ለመቀነስ አስችለዋል
Jul 10, 2026 291
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ሥራዎች የእሳት አደጋና የጎርፍ ተጋላጭነትን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ ማስቻላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ። ኮሚሽኑ የተቋማዊ አቅምን በማጠናከርና የአደጋ ስጋት አመራር ሥርዓቱን በማዘመን በአገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተቋም ለመሆን እየሠራ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን በመገምገም በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይም ዉይይት አካሂዷል። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አሕመድ መሐመድ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ የመዲናዋ የኮሪደር ልማት አደጋን በዘላቂነት ለመቀነስ ዋነኛ መሣሪያ ሆኗል። የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ሥራዎች በመከናወናቸው መሰረታዊ ለውጥ መምጣቱን ጠቁመው፤ በተለይ ቀደም ሲል ለጎርፍ፣ ለእሳት አደጋና ለመሬት መንሸራተት ተጋላጭ የነበሩ አካባቢዎችን ደኅንነታቸው መጠበቁን ገልጸዋል። በተጨማሪም ለተለያዩ ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች፣ የሙያ ምክር አገልግሎት፣ የቴክኒክ ድጋፍ እና የደህንነት መስፈርት ፍተሻዎችን በማከናወን በተቋማት ውስጥ የአደጋ መከላከል ባህል እንዲጠናከር ከፍተኛ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽኑም በቀጣይ የአደጋ መከላከል፣ የምላሽ አቅም ማጠናከር፣ ዲጂታል አሠራርን ማስፋፋት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ትብብር በማጠናከር ለተሻለ የአገልግሎት ውጤት እንደሚሰራም ጠቅሰዋል፡፡ በአራዳ ቅርንጫፍ የኮሚሽኑ ባለሙያ የሆኑት ትዕግስት ተክለአብ ለኢዜአ እንዳሉት፣ ከማኅበረሰቡ ጋር በመደራጀት በብሎክና በወረዳ ደረጃ የቅድመ አደጋ መከላከል ሥራዎች ተከናውነው ጥሩ ውጤት ተመዝግቧል። ሌላው የኮሚሽኑ የአደጋ መከላከል ባለሙያ ማስረሻ ጥላሁን በበኩላቸው፣ አደጋዎች ሲከሰቱ በተቀመጠው መስፈርት መሠረት በፍጥነት በመድረስ አደጋዎችን የመቆጣጠር ሥራ በውጤታማነት መከናወኑን ገልጸዋል። የኮሪደር ልማቱም ለአደጋ ተጋላጭ የነበሩ አካባቢዎችን በማልማት የኮሚሽኑን የአደጋ ቅነሳ ሥራ እንዳገዘ ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ በተፈጥሯዊና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ላይ የመከላከልና የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በስፋት መከናወናቸው ተጠቁሟል፡፡
የሕክምና ማዕከሉ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ አቅም ይፈጥራል
Jul 10, 2026 451
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-"አዲስ የላቀ የሕክምና ማዕከል" ዘመናዊና ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎትን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት የራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ማስፋፊያ የሆነውን "አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል"ን መርቀው ስራ አስጀምረዋል። በምረቃው ወቅት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባደረጉት ንግግር፤ ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜ ጀምሮና በፍጥነት አጠናቆ ለአገልግሎት ማብቃት የከተማ አስተዳደሩ መለያ ባህል መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ከሠራባቸው ማኅበራዊ ዘርፎች መካከል የጤናው ዘርፍ ተጠቃሽ መሆኑንም አክለዋል። በመዲናዋ የነበረውን የጤና አገልግሎት ለማሻሻል የበርካታ አዳዲስ ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች ግንባታ መከናወኑን የጠቀሱት ከንቲባዋ፤ ከአዳዲስ ግንባታዎች ባሻገር በነባር የጤና ተቋማት ላይ ሰፊ የማስፋፊያና የእድሳት ሥራዎች መሠራታቸውን አስታውቀዋል። ይህም ለሕብረተሰቡ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣቱን አመላክተዋል። ከዚህ ቀደም ዜጎች በከፍተኛ ወጪ ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ያገኟቸው የነበሩ የሕክምና አገልግሎቶች አሁን ላይ በከተማዋ መሰጠት መጀመራቸው ሀገሪቱን ከውጭ ምንዛሬና ዜጎችን ደግሞ ከእንግልት መታደጉን ጠቁመዋል፡፡ በጤናው ዘርፍ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል እንድትሆን እያደረጋት እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው "አዲስ የላቀ ሕክምና ማዕከል" የሆስፒታሉን የአገልግሎት አሰጣጥ አድማስ በማስፋት፣ ለተገልጋዮች ምቹና ዘመናዊ ሆኖ መደራጀቱን ጠቅሰዋል፡፡ ማዕከሉ የራሱ የኦክስጅን ማምረቻን ጨምሮ ዘመኑን በዋጁ ልዩ ልዩ ዘመናዊ የሕክምና መሣሪያዎች የተደራጀ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ ቀደም የነበረውን ዘመናዊ እና ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ይበልጥ ለማላቅና አቅምን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል። የማስፋፊያ ማዕከሉ ባለ ሰባት ወለል ሲሆን በ2 ሺህ 60 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ነው፡፡
በሸገር ከተማ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መዘመኑ የህብረተሰቡን እርካታ አሳድጓል
Jul 10, 2026 191
ሸገር፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- በሸገር ከተማ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥን በዘመናዊ መልኩ በማደራጀት፣ የነዋሪዎችን የአገልግሎት እርካታ ደረጃ ማሳደግ መቻሉ ተገለጸ። በሸገር ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተትን በዘላቂነት ለመቅረፍ የአንድ ማዕከል አሰራርን ማስፋፋትና ማዘመን እንደ ዋነኛ የሪፎርም ስራ ተይዞ ሲከናወን ቆይቷል። የከተማው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ መኮንን አምቤ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አሰራሩን ማዘመን ፈጣንና ጥራት ያለው ማህበረሰብ ተኮር አገልግሎትን በተግባር ለማረጋገጥ ማስቻሉን ገልጸዋል። የአገልግሎቱ ዋና ዓላማ የተገልጋዮችን እንግልትና አድካሚ ምልልስ ማስቀረት መሆኑን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፤ አሰራሩ ምቹና ተደራሽ የሥራ ካባቢ በመፍጠር ማህበረሰቡ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ ማስቻሉን አስረድተዋል። በተለይም የአገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ወጪን መቀነስ፣ ለደንበኞች ምቹ ሁኔታን መፍጠር እና የተጠቃሚዎችን እርካታ ማሳደግ መቻሉን ገልጸው፤ ይህም ማህበረሰቡ በመንግስት ላይ ያለው እምነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ያደርጋል ብለዋል። አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽና ፈጣን ለማድረግ በሶስት ዋና ዋና መንገዶች ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አክለው ገልጸዋል። ይህንን ተግባር ይበልጥ ስኬታማ ለማድረግም የአገልግሎት ማዕከላትን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን፤ በዚህ ዓመት ብቻ ሶስት አዳዲስ ማዕከላት ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ተናግረዋል። ወደ ማዕከሉ በመምጣት አገልግሎት ያገኙ ደንበኞች በበኩላቸው፤ በአንድ ማዕከል የሚሰጠው አገልግሎት ከአላስፈላጊ የወጪና የጊዜ ብክነት እንዳዳናቸው ገልጸዋል። ከተጠቃሚዎች መካከል አቶ መሳይ ተሾመ፤ ቀደም ሲል አንድን ጉዳይ ለማስፈጸም በተለያዩ ቦታዎች በመመላለስ ጊዜያቸው ይባክን እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ግን ጉዳያቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ እየተጠናቀቀላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል። አቶ ጀማል መሀመድ በበኩላቸው፤ በዚህ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አማካኝነት ያለምንም እንግልትና ምልልስ የሚፈልጉትን አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል።
ወደ እፎይታ የተሸጋገሩ የአዲስ አበባ ነፍሶች
Jul 10, 2026 204
በተስፋ ሰብዓዊነት ሰገነት ታጅበው፤ ወደ እፎይታ የተሸጋገሩ የአዲስ አበባ ነፍሶች ዝናብ ለብዙ ሰዎች የተፈጥሮ ውበት ነው። ለሌሎች ደግሞ የሰብል ተስፋ፣ የምድር ሕይወትና የአረንጓዴ ወቅት መገለጫ ነው። በአዲስ አበባ አንዳንድ ሰፈሮች ዝናብ ለቤተሰቦች የእፎይታ ሳይሆን የስጋት ምንጭ ነበር። የሚያፈሱ ጣሪያዎች፣ የተሰነጣጠቁ ግድግዳዎች፣ በውኃ የሚጥለቀለቁ ወለሎችና በአደጋ የተከበቡ መኖሪያዎች ለበርካታ ቤተሰቦች የዕለት ተዕለት የጭንቀት ምንጮች ነበሩ። የክረምት ወቅት ሲመጣ የቤት ዕቃዎችን ከደራሽ ጎርፍ ለመጠበቅ ከቦታ ወደ ቦታ ማንቀሳቀስ፣ ሕፃናት ከብርድና ከእርጥበት እንዲድኑ በርካታ ሌሊቶችን ነቅቶ መጠበቅ፣ የእሳትና የጎርፍ አደጋን በፍርሃት መጠበቅ የኑሯቸው አካል ሆኖ ቆይቷል። አንዳንዶች በየጊዜው በሚከሰቱ የእሳት አደጋዎች ስጋት ውስጥ ይኖሩ ነበር። ሌሎች ደግሞ በወንዝ ዳርቻና በተዳፋት ቦታ ስለሚኖሩ ለጤናና ለደህንነት የሚያሰጋ ሁኔታን በየዕለቱ ይጋፈጡ ነበር። ዛሬ ግን ያ ምስል በብዙ ስፍራዎች ተቀይሯል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሪነት በባለሀብቶች፣ በወጣቶች፣ በበጎ ፈቃደኞችና በማህበረሰቡ የጋራ ተሳትፎ የተከናወኑ የቤት ግንባታና የዕድሳት መርሃ ግብሮች ብዙዎችን ከአደገኛ መኖሪያ ወደ ዘመናዊና ምቹ ቤት በማሸጋገር ሰብዓዊ ውጤት እየስገኙ ይገኛል። እነዚህ ፕሮግራሞች የጡብና የሲሚንቶ ሥራ ብቻ አይደሉም። ሰብዓዊ ክብርን የሚያጎናጽፉ፣ ቤተሰቦችን በእፎይታ የሚያኖሩና የሕፃናትን የነገ ተስፋ የሚያለመልሙ ለውጦች ናቸው። በዚህ ተጠቀሚ ከሆኑ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል የልደታ ክፍለ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ቤተልሔም አስፋ ይገኙበታል። እርሳቸው እንደሚገልጹት፣ ከዚህ ቀደም የሚኖሩበት ቤት እጅግ ያረጀ፣ በዝናብ ወቅት በከፍተኛ ሁኔታ የሚያፈስና ለኑሮ የማይመች ነበር። መኖሪያ ቤታቸው በወንዝ ዳርቻና በተዳፋት ቦታ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ልጆቻቸው ለተለያዩ የጤና ችግሮች ይጋለጡ እንደነበርም ያስታውሳሉ። በበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ አማካኝነት መሠረተ ልማት ወደተሟላለትና ለትራንስፖርት አመቺ ወደሆነ አካባቢ መሸጋገራቸው የቤተሰባቸውን ሕይወት እንደለወጠው ይናገራሉ። ዛሬ የዝናብ ወቅት የፍርሃት ምልክት አይደለም፤ የተረጋጋ ሕይወትን በሚያሳይ አዲስ ምዕራፍ ተተክቷል። ለሰው ልጅ መኖር አዳጋች ከነበረ ቤት ወጥተን ዛሬ በክብር ወደምንኖርበት ቤት ገብተናል፤ ይህ ለእኛ አዲስ የሕይወት ምዕራፍ ነው ይላሉ ወይዘሮዋ። የወይዘሮ ቤተልሔም ታሪክ ግን ብቸኛ አይደለም፤ በከተማው በበጎ ፈቃድ ፕሮግራም የተጠቀሙ ብዙ ቤተሰቦች ተመሳሳይ የአኗኗር ለውጥ ታሪክ ባለቤት ናቸው። በከተማው እየተከናወኑ በሚገኙ በጎ ፈቃድ መርሃ ግብሮች ተጠቃሚ የሆኑ በርካታ ዜጎች በሕይወታቸው ላይ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል። ወይዘሮ ገነት ወልደማርያም ያለፉትን ዓመታት ሲያስታውሱ በጠባብና ለኑሮ በማይመች አካባቢ መኖር ለቤተሰባቸው በየቀኑ የሚደገም ፈተና እንደነበር ይናገራሉ። መተላለፊያ የሌለው፣ መሠረተ ልማት ያልተሟላለትና ለልጆች ዕድገት በማይመች አካባቢ ሕይወታቸውን አስቸጋሪ አድርጎት እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን በመንግሥትና በበጎ ፈቃደኞች ትብብር የተገነባላቸው አዲስ መኖሪያ ቤት ከመጠለያነት ባለፈ ለቤተሰባቸው አዲስ የሕይወት ጅማሬ ሆኗል። በደህንነት የሚያድሩበት፣ በክብር የሚኖሩበትና ልጃቸው ያለ ፍርሃት የሚያድግበት ቤት ማግኘታቸውን በትልቅ የህይወት ስጦታነት ይገልጹታል። ይህ የቤት ግንባታ ፕሮግራም የግለሰብ ሕይወትን ብቻ የሚቀይር አይደለም። የቤተሰብ መረጋጋትን፣ የጎረቤት ትስስርንና የማህበረሰብ አንድነትን የሚያጠናክር ሰብዓዊ ኢንቨስትመንት መሆኑን የተጠቃሚዎቹ ታሪክ ያስረዳል። የተገነባው ቤት ብቻ አይደለም፤ ተስፋችንም ነው የሚሉት ደግሞ ሌላኛው የበጎ ፈቃድ ዘመናዊ መኖሪያ መንደር ግንባታ ተጠቃሚ የሆኑት ሀርቆ ሀለጮ ናቸው። በመንግሥትና በበጎ ፈቃደኞች ትብብር የተደረገላቸው ድጋፍ ሕይወታቸውን እንደለወጠው ይናገራሉ። ለእርሳቸው የተገነባው ቤት የመጠለያ ቦታ ብቻ ሳይሆን፣ ማህበረሰቡ ከጎናቸው መቆሙን የሚያሳይ የክብር ማህተም ነው። የአቶ ሀርቆ ሀለጮ ታሪክ የሚያመለክተው አንድ ጠቃሚ እውነት አለ። ሰብዓዊ ድጋፍ በቁሳዊ እርዳታ ብቻ አይለካም። ተጠቃሚዎች እንደሚገልጹት፣ "እኛን የሚያስብ ማህበረሰብ አለ" የሚል ስሜት እንደተሰማቸውም ነው የሚናገሩት። ይህ ደግሞ ከግንባታው በላይ የሚዘልቅ ግዙፍ ሰብዓዊ ዋጋ አለው። በተመሳሳይ ወይዘሮ ወጋየሁ ወርቁ የቀድሞ መኖሪያቸው በመጨናነቅና በየጊዜው በሚከሰቱ የእሳት አደጋዎች ስጋት የተሞላ ሕይወት ይመሩ እንደነበር ያስታውሳሉ። አሁን ግን በአዲሱ መኖሪያቸው የሚሰማቸው ስሜት ከፍርሃት ይልቅ መረጋጋት፣ ከጭንቀት ይልቅ ተስፋ ነው። የእነዚህ ቤተሰቦች ታሪክ በአዲስ አበባ የተከናወኑ የበጎ ፈቃድ ተግባራት የሚለኩት በተገነቡ ቤቶች ብዛት ብቻ ሳይሆን፣ በተለወጡ ሕይወቶች እና በተረጋጉ የአኗኗር ዘይቤዎችም ጭምር መሆኑን በግልጽ ያሳያል። የሰብዓዊነት ባህል ሲደረጅ ከሕንፃ ግንባታ የተሻገረን ትውልድ ያንፃል። በአዲስ አበባ የተከናወኑና የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ተግባራት በቤት ግንባታ ብቻ የሚወሰኑ አይደሉም። የከተማዋ የምገባ ማዕከላት በየዕለቱ ለአረጋውያን፣ ለአቅመ ደካሞችና ለሌሎች ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች የሚቀርቡ የምግብ ድጋፍ፣ የቤት ዕድሳትና ግንባታ፣ እንዲሁም የመኖሪያ ቤት ባለቤትነትን የሚያረጋግጡ ፕሮግራሞች በአንድ ላይ ተደምረው ለሺዎች ዜጎች አዲስ የሕይወት ምዕራፍ እየከፈቱ ነው። በየዓመቱ በሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሮች ወጣቶች ጉልበታቸውን፣ ባለሀብቶች ገንዘባቸውን፣ የማህበረሰብ አባላት ጊዜያቸውንና ሙያቸውን በማበርከት ሰብዓዊ አገልግሎትን ከንቅናቄ ወደ ባህል እንዲያድግ አስችለዋል። በዚህም ከቤት ግንባታ ባሻገር የመተሳሰብና የመረዳዳት ዕሴቶች በከተማዋ ይበልጥ እንዲጠናከሩ አድርገዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አስራት ንጉሴ እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል በከፊል የቤት ዕድሳት ላይ ያተኮረው አሠራር በአሁኑ ወቅት የከተማዋን የልማት አቅጣጫ በሚመጥን መልኩ ወደ ሙሉ የቤት ግንባታ ተሸጋግሯል። ይህም ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች፣ አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ አቅመ ደካሞችና ወላጅ አልባ ሕፃናት በቀዳሚነት ተጠቃሚ አድርጓል። በእርግጥም ልማት የሚለካው በሚገነቡ ሕንፃዎች ከፍታ ብቻ አይደለም። በዜጎች ሕይወት ላይ በሚመጣ ለውጥ እንጂ። በበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሮች አማካኝነት ከሚያፈሱ ጎጆዎች ወደ ዘመናዊ መኖሪያዎች የተሸጋገሩ ቤተሰቦች፣ በምገባ ማዕከላት የዕለት ምግብ ዋስትና ያገኙ አረጋውያን፣ በተለያዩ ማህበራዊ ፕሮግራሞች ተደግፈው ተስፋን ያገኙ ዜጎች የዚህ እውነታ ሕያው ማሳያዎች ናቸው። ወይዘሮ ቤተልሔም፣ ወይዘሮ ገነት ወልደማርያም፣ አቶ ሀርቆ ሀለጮና ወይዘሮ ወጋየሁ ወርቁ ያካፈሉን ተሞክሮ የሚያሳየው አንድ ግልጽ መልዕክት ለሰው ልጅ ክብር የሚሰጥ መኖሪያ፣ የተረጋጋ የምግብ ዋስትናና የማህበረሰብ ድጋፍ ሲገናኙ የሚለወጠው ቤት ብቻ አይደለም፤ ሕይወት መሆኑን እንጂ። ስለዚህ በአዲስ አበባ የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ተግባራት ከማህበራዊ ድጋፍ ባለፈ የከተማዋን የሰብዓዊ ልማት አቅጣጫ የሚያንፀባርቁ ናቸው። ከሚያፈስ ጎጆ ወደ ክብር መኖሪያ የተጀመረው ጉዞ፣ የጡብና የሲሚንቶ ታሪክ ሳይሆን የሰውን ክብር የመጠበቅ፣ ተስፋን የማደስና የማህበረሰብ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ እየቀጠለ ይገኛል።
ኢኮኖሚ
በከተማው በአዲሱ በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር ተገብቷል
Jul 10, 2026 77
ሀዋሳ፤ ሐምሌ3/2018(ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በአዲሱ በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር መገባቱን የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በከተማው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት እና የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች ለመመለስ ትኩረት መሰጠቱም ተመላክቷል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ መልኩ ማርቆስ ለኢዜአ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በከተማው ከ7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የዕቅዱን 102 ፐርሰንት ማሳካት ተችሏል፡፡ በ2019 ግብር ዘመን12 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር መገባቱን ገልፀው ከሐምሌ 1 ጀምሮ ገቢ የመሰብሰብ ሥራው መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት የገቢ አሰባሰብ ሥራው በቴክኖሎጂ መታገዙ፣ የባለሙያዎች አቅም መገንባቱና የገቢ ምንጮችን ማስፋት በመቻሉ ገቢን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል፡፡ በተያዘው የግብር ዘመንም የተጨማሪ እሴት ታክስ ገቢን የማሳደግ፣ ከቅጥር የሚገኝ ገቢን እና የአከራይ ተከራይ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ መልኩ አስረድተዋል፡፡ በከተማ አስተዳደሩ ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ ከጥሬ ገንዘብ ንክኪ ነፃ የሆነ የገቢ አሰባሰብ ሥርዐት በመዘርጋት በባንክ የክፍያ ማረጋገጫ ብቻ ገቢ እየተሰበሰበ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ ዓመት ጀምሮም የባንክ ክፍያን በማስቀረት በቴሌ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ እና ሌሎች ዘመናዊ የክፍያ አማራጮች ብቻ ገቢን ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ቅድመ ዝግጅቶች ተደርገው ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል፡፡ በከተማው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት እና የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች ለመመለስ ትኩረት መሰጠቱንም አመልክተዋል። ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ባለው የገቢ አሰባሰብ ሂደት ግብር ከፋዮች ግብራቸውን እየከፈሉ እንደሚገኙም አቶ መላኩ ጠቁመዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል በታቦር ክፍለ ከተማ በሸቀጣሸቀጥ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩት ወይዘሮ መስከረም አስፋው በየዓመቱ ግብራቸውን በወቅቱና በታማኝነት የመክፈል ልምድ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ከዜጎች የሚሰበሰበው ገቢ በከተማዋ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች እንደሚውል በመረዳታቸው በራሳቸው ተነሳሽነት ግብራቸውን በወቅቱ እንደሚከፍሉ ተናግረዋል፡፡ በግብር ሰብሳቢው አካል የሚሰጠው አገልግሎት በቴክኖሎጂ የታገዘና ከጊዜ ወደ ጊዜ ቅልጥፍናው እየጨመረ የመጣ በመሆኑ ያለ እንግልት ግብራቸውን በቀላሉ መክፈል እንደቻሉም ጠቁመዋል፡፡ በሀዋሳ መናኸሪያ ክፍለ ከተማ በእንግዳ ማረፊያ የአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ኢያሱ በገጄ ግብር ለሀገራችን የምንከፍለው የዜግነት ግዴታችን ነው ብለዋል፡፡ የከተማዋ የልማት ሥራ ጥቅሙ ለነዋሪው እንደሆነ ጠቅሰው ልማቱ እንዲፋጠን ግብራቸውን በአግባቡና በወቅቱ በመክፈል ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ቢሮው የአገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የተገልጋዩን እርካታ ማሳደግ ችሏል
Jul 10, 2026 97
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ በመደገፍና አዳዲስ አሰራሮችን በመዘርጋት የተገልጋዩን እርካታ ማሳደግ መቻሉን አስታወቀ። ቢሮው በ2018 በጀት ዓመት የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ያከናወናቸውን ተግባራት፣ የቢሮውን የለውጥ ጉዞና የተገኙ ስኬቶችን የሚያሳይ ኤግዚቢሽንም በዛሬው ዕለት በይፋ ከፍቷል። የቢሮው የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ ቢሮው የግብር ከፋዩን እንግልት ለመቀነስና ግልጽነትን ለመፍጠር በርካታ የሪፎርም ስራዎችን አከናውኗል። ወደ 24 የሚጠጉ አሰራሮች መዘርጋታቸውን ይህንንም በማሳተም ለተገልጋዩ ማህበረሰብ ተደራሽ መደረጉንና ከግብር ከፋዩ ሕብረተሰብ ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት መሰራቱን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት በቢሮው ስር ባሉ 17ቱም ቅርንጫፎች የሚገኙ ከሰባት ሺህ በላይ ሰራተኞችን መቆጣጠር የሚያስችል የቴክኖሎጂ አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም የአገልግሎት አሰጣጡ እንዴት እየተከናወነ እንደሚገኝ ዋና ቢሮ ሆኖ በቀጥታ መከታተል የሚያስችል የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋቱንም ጠቁመዋል፡፡ በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ የንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዘሃራ መሐመድ በበኩላቸው፤ ከቢሮው ጋር እየተደረገ ያለው የተቀናጀ አሰራር አዎንታዊ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ በተደረገው የጋራ ጥረትና ቅንጅታዊ አሰራር፣ ከነጋዴው ማህበረሰብ የተነሱ የተለያዩ ቅሬታዎችን በጋራ በመገምገም 620 ለሚሆኑ ነጋዴዎች ለገጠሟቸው ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
ተምሳሌቶቹ የቢሾፍቱ ከተማ የሌማት ትሩፋት ተጠቃሚዎች
Jul 10, 2026 160
የሌማት ትሩፋት ሀገራዊ ውጤት እና በመርሃ ግብሩ ህይወታቸውን ያሻሻሉ የቢሾፍቱ ነዋሪዎች ለብዙ ኢትዮጵያውያን ወተት፣ እንቁላል፣ ማርና ሥጋ በምግብ ገበታ የማይገኙ፣ ለረጅም ዓመታት የቅንጦት ያህል የሚታዩና በቂ ምርት ባለመኖሩም በገበያ ላይ በስፋት የማይገኙ ነበሩ። ይህንን እውነታ ለመቀየርና የዜጎችን የሥርዓተ ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመረው የሌማት ትሩፋት ሀገራዊ መርሃ ግብር ዛሬ ላይ ትልቅ ተስፋና ተጨባጭ ውጤት እያሳየ ይገኛል። ቀደም ሲል ትኩረት አጥቶ የነበረውን የእንስሳት ተዋጽኦ ልማት በቅንጅትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ ረገድ በአካባቢው ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል። በግብርና ሚኒስቴር መረጃ መሠረት መርሃ ግብሩ ከመጀመሩ በፊት የነበረው 7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ሊትር የወተት ምርት ዘንድሮ 15 ነጥብ 7 ቢሊዮን ሊትር መድረሱ፣ ቀደም ሲል በዓመት ይሰራጭ የነበረው የዶሮ ጫጩት ከ26 ሚሊዮን ወደ 184 ሚሊዮን ማደጉ እንዲሁም የእንቁላል ምርት ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ወደ 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ከፍ ማለቱ የዚሁ አገራዊ ስኬት ማሳያዎች ናቸው። ይህ የተጀመረው አበረታች ሂደት እንደ ወተት፣ ማር፣ ሥጋ፣ አሳ እና እንቁላል ያሉ ምርቶች የቅንጦት ሳይሆኑ የዜጎች የዕለት ተዕለት የሥርዓተ ምግብ አካል እንዲሆኑ በማስቻል ረገድም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በቢሾፍቱ ከተማና አካባቢዋ ለሚኖሩ በርካታ ዜጎች የአመጋገብ ሥርዓትን ከመቀየር ባለፈ፣ የኢኮኖሚ አቅማቸውን የለወጠ የሕይወት ጉዞን ፈጥሮላቸዋል። አቶ ከፈለኝ ጫላ ቀደም ሲል በመንግሥት ተቋም ተቀጥረው የሚሠሩ መደበኛ ሠራተኛ ነበሩ። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ላይ ዜጎች እንዲሳተፉ ጥሪ ሲቀርብ ግን የቀደማቸው አልነበረም። በተመቻቸላቸው የብድር አገልግሎት በመታገዝ በአንድ የወተት ላም ሥራቸውን ጀመሩ። ዛሬ ላይ ግን ታሪካቸው ሙሉ በሙሉ ተቀይሯል። የነበራቸውን ብቸኛ ላም ተንክባክበውና አርብተው በአሁኑ ወቅት የወተት ላሞቻቸውን ቁጥር 15 ማድረስ ችለዋል። "መንግሥት ያደረገልኝ ተከታታይ ድጋፍና ክትትል ለዚህ ውጤት እንድበቃ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቶልኛል" ይላሉ አቶ ከፈለኝ። የራሳቸውን ኑሮ ከመቀየር ባለፈ፣ የሚያመርቱትን ወተት ለአካባቢው ማኅበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን በማረጋጋት ረገድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። በተጨማሪም በመስኩ ለሌሎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል። ሌላኛው በዚሁ መርሃ ግብር ሕይወታቸው የተቀየረው ሥራ ፈጣሪ አቶ ጌቱ ብሩ ናቸው። እሳቸው ደግሞ በተቀናጀ የዶሮና የዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ላይ ነው የተሰማሩት። የሌማት ትሩፋት ያመጣላቸው በረከት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከመጥቀም አልፎ የንግድ አድማሳቸውን አስፍቶላቸዋል። ከልማቱ በሚያገኙት የምርት ውጤት የራሳቸውን ሆቴል መክፈት የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም አዲስ የሥራ ዕድል ፈጥረዋል። "ለሆቴላችን የምግብ ግብዓት የሚሆነውን ምርት የምናቀርበው ከራሳችን የዶሮና የዓሣ እርባታ ማዕከል ነው" የሚሉት አቶ ጌቱ፣ ዘርፉ ሰፊና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት የሚቻልበት መሆኑን ይመሰክራሉ። አቶ ጌቱ እቅዳቸው እዚህ ላይ ብቻ አያበቃም፤ በቀጣይ የሌማት ትሩፋት ምርቶችን እሴት ጨምረው ለከተሞች ከማቅረብ ባለፈ ወደ ውጭ ሀገር ለመላክና ለሀገር የውጭ ምንዛሬ የማስገኘት ውጥን አላቸው። ሌሎችም በዚህ ሥራ ላይ ቢሰማሩ ከራሳቸው አልፈው ሀገርንና ወገንን መለወጥ እንደሚችሉም ነው የጠቆሙት። በተመሳሳይ በዶሮ እርባታ ሥራ ላይ የተሰማሩት አቶ ደረጄ አበበ መርሃ ግብሩ ከፍተኛ ገቢ እንዲያገኙ እንዳስቻላቸው ይናገራሉ። የዶሮ እንቁላል ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለአካባቢው ማኅበረሰብ በስፋት በማቅረብ የኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም የበኩላቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)፥ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበትና የዜጎችን የምግብና ሥርዓተ ምግብ አቅም እያሳደገ የሚገኝ ኢኒሼቲቭ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ሀገራዊ ጥረት ለማሳካት የእንስሳት ሀብት ልማት ዘርፍ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ጠቅሰዋል። አክለውም፤ ኢኒሼቲቩ በቤተሰብ ደረጃ የዶሮ እርባታን ባህል እንዲሆን በማድረግ፣ በተለይም ሕፃናትና እናቶች የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ በማስቻል ረገድ መሠረታዊ ለውጥ እያመጣ መሆኑንና ምርቶችን በስፋት ለገበያ እንዲቀርቡ በማስቻል ረገድ ትርጉም ያለው ውጤት ማምጣቱን ገልጸዋል።
በጎንደር ከተማ ወደ 49 ሺህ ለሚጠጉ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ተፈጥሯል
Jul 10, 2026 186
ጎንደር፤ ሃምሌ 3/2018 (ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ አስተዳደር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 49 ሺህ ለሚጠጉ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፍጠር መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ የስራና ክህሎት መምሪያ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ሥራና ክህሎት መምሪያ ያለፈውን በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ትውውቅ መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ አካሄዷል። የመምሪያው ኃላፊ አቶ አበበ ላቀው በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በከተማዋ በተካሄዱ የኢንዱስትሪ፣ የከተማ ግብርና፣ የንግድና አገልግሎት ዘርፎች ለወጣቱ የሥራ ዕድል ለመፍጠር በትኩረት ተሰርቷል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ለ44 ሺህ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ በተደረገ ጥረት፣ ከ48 ሺህ 900 በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ከዕቅድ በላይ መፈጸም መቻሉን ገልፀዋል። ከዕቅድ በላይ ማስመዝገብ የተቻለውም በተገኘው ሰላም ባለሀብቱ ተረጋግቶ ወደ ልማት በመግባቱና አመራሩና ባለሙያው የተጠናከረ ድጋፍ በማድረጋቸው መሆኑንም አብራርተዋል። ከአበዳሪ ተቋማት ጋር በመተባበርም ለ2 ሺህ 689 ኢንተርፕራይዞች 665 ሚሊዮን ብር ብድር በማሰራጨት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። የሥራ ዕድሉን መፍጠር የተቻለውም በኮንስትራክሽን፣ በከተማ ግብርና፣ በአነስተኛ ንግድና ሌሎች የሥራ ዘርፎች መሆኑን አስረድተዋል። በተጨማሪም መምሪያው ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጎን ለጎንም ለ856 ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ በማድረግ ያሉባቸውን ችግሮች ለመፍታት ጥረት ማደረጉን ገልጸዋል። ከጎንደር ከተማ አስተዳደር መሬት መምሪያ ጋር በመተባበር በኮሪደር ልማት ለተነሱ 334 ግለሰቦች የመስሪያና የመሸጫ አገልግሎት መስጫ ሼድ በማስገንባት ማስረከብ መቻሉንም አክለዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የጎንደር ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማይ ልጅዓለም በበኩላቸው፤ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በሥራ ዕድል ፈጠራ አበረታች ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። ይህም የከተማው አስተዳደር የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራን በዋነኝነት ይዞ በየጊዜው እየገመገመና የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ በመስራቱ የመጣ ውጤት መሆኑን አስረድተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በዞኑ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ ቀልጣፋና ግልጽነት የሰፈነበት አሰራርን በማረጋገጥ እያገዘ ነው
Jul 10, 2026 141
መቱ፤ ሐምሌ 3/2018 (ኢዜአ):- የኢሉአባቦር ዞን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ ቀልጣፋና ግልጽነት የሰፈነበት አሰራርን በማረጋገጥ የህብረተሰቡን እንግልት እየቀነሰ መሆኑ ተገለጸ። የኢሉአባቦር ዞን ያዮ ወረዳ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በዛሬው ዕለት ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል። የኢሉአባቦር ዞን አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ፤ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ማህበረሰቡን በታማኝነትና በቅንነት ለማገልገል ታልሞ የተቀረጸ ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በዞኑ ወደ ስራ የገቡ ማዕከላትም የህብረተሰቡን የአገልግሎት ተደራሽነት የሚያሰፋ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አሰራርን እያሰፈኑ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የተገልጋዩን ድካምና እንግልት ማስቀረት እያስቻለ መሆኑንም ገልጸዋል። በያዮ ወረዳ ስራ የጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 32 የስራ ክፍሎችን በአንድ ላይ ያካተተ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ በቀጣይም አሰራሩን በሁሉም የዞኑ ወረዳዎች ለማስፋፋት በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቀዋል። ከወረዳው ነዋሪዎች መካከል ቄስ ሳሙኤል ደምሴና ወይዘሮ ወርቄ ተፈራ፤ ማዕከሉ የተገልጋዩን መጉላላት የሚያስቀርና የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቱን የሚያሻሽል በመሆኑ ስራ መጀመሩ አስደስቷቸዋል። ብልሹ አሰራሮችን በመቀነስ ረገድ መንግስት እየወሰዳቸው የሚገኙት መሰል እርምጃዎች አበረታች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። ወይዘሮ ገላኔ ኮርሳና አቶ ጀማል ኢብራሂም በበኩላቸው፤ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ህዝቡን ከምልልስና ከተጨማሪ ወጪ የሚታደግ መሆኑን አንስተዋል። የመንግስት አገልግሎት ሰጪ መስሪያ ቤቶችም ከተለመደውና ለቅሬታ ከሚዳርጉ ብልሹ አሰራሮች በመላቀቅ፣ ማህበረሰቡን በታማኝነት የማገልገል ባህላቸውን ሊያሳድጉ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢንቨስትመንት የቁልፍ መሰረተ ልማት ተቋማትን ደኅንነት መጠበቅ የሚያስችል አቅም ፈጥሯል
Jul 10, 2026 193
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት የዜጎችንና የቁልፍ መሰረተ ልማት ተቋማትን ደኅንነት መጠበቅ የሚያስችል አቅም መፍጠሩን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። ዓለም አቀፉ የፓርላማ የመረጃ ደኅንነት ፎረም ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ስብሰባውን በአዲስ አበባ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ማካሄድ ጀምሯል። በመድረኩ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም፣ የሳይበር ደኅንነት፣ ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መሰል ዓለም አቀፍ አሳሳቢ ጉዳዮች ላይ በስፋት ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የደኅንነት ፈተናዎችን በአፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥና በአጋርነት መርህ ላይ የተመሰረተ በርካታ ስኬታማ ሥራዎችን እያከናወነች ነው። በዚህም ቀጣናዊ ጠንካራ የትብብር ማዕቀፎችን በመዘርጋት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና በሰዎች መነገድ ወንጀልን ለመከላከል እየሰራች መሆኗን ገልጸዋል። ቀጣናዊ ሰላምና ደኅንነትን በማስጠበቅ፣ የሽብር ቡድኖችን እንቅስቃሴ ከማክሸፍ ባሻገርም፣ ልማትን በማፋጠን ድኅነትና ሥራ አጥነትን በጋራ ለመቀነስ አስደናቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን አንስተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂክ ኢንቨስትመንት የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የዲጂታል መሠረተ ልማትና ሳይበር ደኅንነት አቅምን በማጎልበት የዜጎችንና ቁልፍ ብሔራዊ ተቋማትን ለመጠበቅ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያካሄደችው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም አካታች፣ ነፃና ፍትሐዊ እንዲሁም ለሕገ-መንግሥታዊ አስተዳደርና ለሕግ የበላይነት ያላትን ቁርጠኝነት ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት ዓለም እያጋጠሟት ያሉ ስጋቶች ውስብስብና በፍጥነት የሚቀያየሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። መንግሥታትም የሳይበር ወንጀሎችን ለመከላከል የመረጃ ልውውጥና ሕጋዊ ማዕቀፎችን በማጣጣም ትብብራቸውን ማሳደግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። የኢትዮጵያና አሜሪካ የጤና ዘርፍ አጋርነት ውጤታማ ተግባራትን እያከናወኑ ነው ያሉት አምባሳደሩ፤ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመዋጋትም በትብብር እየተሰራ ነው ብለዋል። የፎረሙ መስራችና ሊቀመንበር ሮበርት ፒተንገር ፤ ፎረሙ ኢትዮጵያ ለልማትና ዴሞክራሲ ያላትን ቁርጠኝነት እንዲሁም የመሪዎቿን ርዕይ ለመላው ዓለም ለማሳየት ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ሰፊ ተጠቃሚነትን ለማግኘት የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው
Jul 10, 2026 255
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ሰፊ ተጠቃሚነትን ለማግኘት የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ገለጹ። የፓርላማ መረጃና ደህንነት ፎረም በመካሄድ ላይ ነው። ኢትዮጵያ ደኅንነቱ የተረጋገጠ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ተጠቃሚነቷን ለማሳደግ በትኩረት እየሠራች መሆኑ በፎረሙ ላይ ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ከዘርፉ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። በሰው ሰራሽ አስተውሎት ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ መሰረተ ልማቶች እየተገነቡ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ዘርፉን ለቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ ለሰላም ግንባታ እና ለመንግሥታዊ አገልግሎቶች ጥቅም ላይ እያዋለች እንደምትገኝ አመልክተዋል። ኤአይን በሕግ ለመምራት እና ሥጋቶችን ለመቀነስ የሚያስችሉ የሕግ ዝግጅቶች በስፋት በመከናወን ላይ እንደሚገኙም ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወቅታዊ የደኅንነት ሥጋቶች ላይ ያተኮሩ ጽሑፎች በፎረሙ ላይ በመቅረብ ላይ እንደሚገኙ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ ያመለከታል።
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ መስተንግዶ እንድናገኝ አስችሎናል- ተገልጋዮች
Jul 10, 2026 240
ወልቂጤ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ጊዜና ገንዘብ ከመቆጠብ ባለፈ ቀልጣፋ መስተንግዶ እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት በመላ ሀገሪቱ ተግባራዊ የተደረገው የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት ሆኗል። አገልግሎቱ የተበታተኑ የመንግስት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕቀፍ እና በአንድ ማእከል ለዜጎች የዲጂታል አገልግሎት የሚሰጥበት ዘመናዊ አሰራር ሲሆን ጊዜንና ወጭን ከመቆጠብ ባለፈ ለመልካም አስተዳደር ችግር ሁነኛ መፍትሄ ሆኗል። በአንድ ማእከል በርከት ያሉ አገለግሎቶች የሚሰጡበት የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት እየተስፋፋና በዜጎች ዘንድ በብዛት እየተለመደ መጥቷል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም በአጭር ጊዜ ውስጥ የተለያዩ ከተሞች ሰባት የመሶብ የአንድ ማዕከላት ተከፍተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ። በክልሉ የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት ከሚሰጥባቸው ማእከላት መካከል የኢዜአ ሪፖርተር በወልቂጤ ከተማ ሲገለገሉ ያገኛቸውን ደንበኞች አነጋግሯል። ከተገልጋዮቹ መካከል ወይዘሮ ብርዝነሽ ጋሚ እና አቶ ሃብታሙ እሸቴ፤ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ጊዜና ገንዘብ ከመቆጠብ ባለፈ ቀልጣፋ መስተንግዶ እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል። በማእከሉ ዲጂታል ፋይዳ ለማውጣት እና የፖስታ አገልግሎት ሲጠቀሙ ያገኘናቸው ወይዘሮ ብርዝነሽ፣ በማእከሉ በፍጥነት እና በእንክብካቤ ጉዳያቸውን ፈፅመው መጨረሳቸውን ተናግረዋል። ለንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት የመጡት አቶ ሃብታሙ እሸቴ በበኩላቸው፤ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለህዝብ ተብሎ የተሰራ ለመልካም አስተዳደር ችግር ሁነኛ መፍትሄ ያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።፡ የውክልና አገልግሎት ለመስጠት መጥተው ጉዳያቸውን በፍጥነት ማጠናቀቃቸውን የተናገሩት አቶ አብዱልፈታ ስራጅ፤ አገልግሎቱ እንግልትና መጉላላትን ያስቀረ አስደናቂ አሰራር መሆኑን ገልጸዋል። በማእከሉ የህግ ባለሙያ የሆኑት ወይዘሮ ግሩምነሽ ኤልያስ፤ በቴክኖሎጂ የተደራጀው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከዚህ ቀደም ሁለትና ሦስት ቀናት ይፈጅ የነበረውን ጉዳይ በደቂቃዎች በማጠናቀቅ ፈጣን ምላሽ እየሰጠ ነው ብለዋል። የወልቂጤ ከተማ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ሄኖክ ወልደገብርኤል በበኩላቸው፣ ማእከሉ ለማህበረሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በማእከሉ አሁን ላይ የሰባት የተለያዩ ተቋማት 24 አገልግሎቶች እየተሰጡበት መሆኑን ጠቁመው በቀጣይ የመጨመር እቅድ መኖሩን ተናግረዋል።
ስፖርት
የአውሮፓ ኃያላን ፍጥጫ፤ የስፔንና የቤልጂየም ተጠባቂ የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ
Jul 10, 2026 524
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- 23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን ከቤልጂየም ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ በሎስ አንጀለስ ስታዲየም ይካሄዳል። ስፔን በ16ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ፖርቹጋልን 1 ለ 0 አሸንፋለች። የአንድ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ስፔን በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ ለሰባተኛ ጊዜ ለሩብ ፍጻሜ አልፋለች። ተጋጣሚዋ ቤልጂየም ከአዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችውን አሜሪካን 4 ለ 1 በመርታት ለአራተኛ ጊዜ ወደ ሩብ ፍጻሜ መግባት ችላለች። ሁለት ሀገራት በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ነው። ሜክሲኮ እ.አ.አ በ1986 ባዘጋጀችው 13ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በሩብ ፍጻሜው ተገናኝተው ቤልጂየም በመለያ ምት 5 ለ 4 በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜ አልፋለች። እ.አ.አ በ1990 በጣልያን በተካሄደው 14ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በምድብ አምስት ተገናኝተው ስፔን ቤልጂየምን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ሁለቱ ሀገራት ከ36 ዓመታት በኋላ በዓለም ዋንጫው መድረክ ተገናኝተዋል። ሀገራቱ በውድድሮች እና በወዳጅነት ጨዋታዎች 23 ጊዜ ተገናኝተው ስፔን 12 ጊዜ ድል ሲቀናት ቤልጂየም በአምስት ጨዋታዎች አሸንፋለች። በቀሪ ስድስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ስፔን በ23ቱ ጨዋታዎች ላይ 46 ጎሎችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ቤልጂየም 22 ግቦችን አስቆጥራለች። የ29 ዓመቱ አጥቂ ሚኬል ኦያርዛባል ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የስፔን የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። የ33 ዓመቱ የፊት መስመር ተሰላፊ ሮሜሎ ሉካኩ ለቤልጂየም በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ሶስት ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሊያንድሮ ትሮሳርድ እና ቻርልስ ደ ኬቴላሬ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል። በፊፋ የዓለም ሀገራት የእግር ኳስ ደረጃ ስፔን 3ኛ፣ ቤልጂየም ደግሞ 8ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ላሚን ያማል እና ሮድሪ ከስፔን፣ ኬቨን ደ ብሮይን እና ሮሜሎ ሉካኩ ከቤልጂየም በጨዋታው ልዩነት ይፈጥራሉ ተብለው የሚጠበቁ ናቸው። ሁለቱ የአውሮፓ ኃያላን ሀገራት በዛሬው ጨዋታ አዝናኝ እና ማጥቃት ላይ የተመሰረተ የጨዋታ እንቅሰቃሴ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። የዛሬው ጨዋታ አሸናፊ በግማሽ ፍጻሜው ከፈረንሳይ ጋር ይጫወታል። ፈረንሳይ ትናንት ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።
ፈረንሳይ ሞሮኮን በመርታት ለግማሽ ፍጻሜ አለፈች
Jul 9, 2026 849
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ማለፍ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በቦስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኪሊያን ምባፔ በ60ኛው እና ኡስማን ዴምቤሌ በ65ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ምባፔ በ28ኛው ደቂቃ ፍጹም ቅጣት ምት ስቷል። ፈረንሳይ በጨዋታው ፍጹም ብልጫ ወስዳለች። የተደራጀ መከላከል እና የመልሶ ማጥቃት የአጨዋወት ስልት የተከተለችው ሞሮኮ ግልጽ የግብ እድሎችን መፍጠር ተስኗታል። የ27 ዓመቱ ኪሊያን ምባፔ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ስምንት በማድረስ ከአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ ጋር በጎል እኩል በመሆን ሶስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል ብልጫ ወስዶ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ይገኛል። በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ 20 ጎሎች ከመረብ ላይ በማሳረፍ በምንጊዜም ከፍተኛ አስቆጣሪነቱ ከሜሲ (21 ጎል) በአንድ አንሶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ምባፔ በዓለም ዋንጫው የጥሎ ማለፍ ምዕራፍ 12ኛ ጎሉን በማስቆጠር በውድድሩ አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል። ለብሔራዊ ቡድኑ 64ኛ ጎሉን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ምባፔ በ77ኛው ደቂቃ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ ወጥቷል። የባለንዶር ባለቤቱ ኡስማን ዴምቤሌ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አምስተኛ ጎሉን አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ፈረንሳይ ግማሽ ፍጻሜውን የተቀላቀለች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች። በዓለም ዋንጫው ለግማሽ ፍጻሜ ስታልፍ የአሁኑ ለሰባተኛ ጊዜ ነው። ፈረንሳይ በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ሞሮኮ የዓለም ዋንጫ ጉዟዋ ሩብ ፍጻሜው ላይ አብቅቷል። ለተከታታይ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የመግባት ህልሟ ሳይሳካ ቀርቷል። በሩብ ፍጻሜው ላይ አፍሪካን የወከለችው ብቸኛ ሀገር ሞሮኮ ከውድድሩ ተሰናብታለች። የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር ከተሳተፉ 10 ቡድኖች መካከል የተሻለ ርቀት መጓዝ ችላለች። ሞሮኮ በ22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ የአፍሪካ ሀገር መሆኗ የሚታወስ ነው። በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ አፍሪካ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ 10 ሀገራት አሳትፋለች።
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ዋንጫን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ አነሳ
Jul 9, 2026 462
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2 /2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 0 አሸንፏል። ረፋድ ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጋናዊው አጥቂ ኮንኮኒ ሃፊዝ በ47ኛው እና በየነ ባንጃ በ99ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጨዋታውን በርካታ ደጋፊዎች በስታዲየም በመገኘት ተከታትለውታል። ውጤቱን ተከትሎ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ዋንጫን አንስቷል። በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ46 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዞ ላጠናቀቀው ወልዋሎ የዛሬው ድል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ነው። የኢትዮጵያ ዋንጫ ድሉ በ1948 ዓ.ም ለተመሰረተው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ትልቅ ከሚባሉ ስኬቶች መካከል የሚጠቀስ ነው። ሲዳማ ቡና በአህጉራዊ ውድድር ተሳትፎውን በማረጋገጡ ምክንያት፣ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የውድድር ደንብ መሰረት ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን ተከትሎ የጨዋታውን ውጤት ሳይጠብቅ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት መሳተፉን ማረጋገጡ የሚታወስ ነው። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና ለተከታታይ ዓመት ለኢትዮጵያ ዋንጫ ቢደርስም ዋንጫውን ለመጀመሪያ ጊዜ የማሸነፍ ህልሙን ማሳከት አልቻለም። የዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ሲዳማ ቡና፣ ዓመቱን በሁለት ዋንጫ የማጠናቀቅ ፍላጎቱ ሳይሳካ ቀርቷል። ሲዳማ ቡና ፕሪሚየር ሊጉን ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ያነሳ ሲሆን ይህን ተከትሎም በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን አረጋግጧል። ሁለቱ ቡድኖች በቀጣዩ ዓመት ኢትዮጵያን በአህጉራዊ የክለብ ውድድሮች ላይ ወክለው ይሳተፋሉ። በ1937 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮጵያ ዋንጫ የ80 ዓመት ታሪክ ያለው አንጋፋ ውድድር ነው።
በክልሉ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናማና አምራች ዜጋን የማፍራት ሥራው ይጠናከራል
Jul 9, 2026 364
ሆሳዕና፤ ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦በማዕክላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ባህል በማድረግ ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራትና አብሮነትን ለማሳድግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠናከር የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሠራተኞችና ሃላፊዎች የተሳተፉበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርሀግብር ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል። የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ባህል በማድረግ ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራትና የአብሮነት እሴትን ለማጠናከር እየተሰራ ነው። በየአካባቢው የሚካሄደው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናማና አምራች ዜጋ ለማፍራት ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፣ የእርስ በርስ ግንኙነትን በማሳደግ በኩል ፋይዳው የጎላ በመሆኑም ስፖርቱን ለማስቀጠል ይሰራል ብለዋል። የዛሬው መርሀግብር ስፖርትን ባህል የማድረግ ሥራን ከማጠናከር ባለፈ ወጣቶች በበጎ ፍቃድ ሥራ እንዲሳተፉ ያለመ እንደሆነና መሰል መርሀግብሮችም በየአካባቢው እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የቢሮው ምክትል ሀላፊና የስፖርት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሰይፈ አለሙ በበኩላቸው እንደገለጹት በስፖርት ልማት ዘርፉ ክልሉ ያለውን አቅም ለይቶ መጠቀም የሚያስችል ሥራ እየተሰራ ነው። ለእዚህም ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራዎችን ለማስፋትና በሁሉም የስፖርት ዘርፍ ታዳጊና ተተኪ ስፖርተኞችን በማፍራት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አመልክተዋል። በተያዘው ክረምት ክልሉን የሚወክል የሰርከስ ቡድን ለማቋቋም መታቀዱን የገለጹት ሀላፊው የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችም ብቃት ያላቸው ወጣቶችን ለመለየት አይነተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ከተሳተፉት የማህበረሰብ ክፍሎች መካከል አቶ ብዙአየሁ ሀይሌ እና አቶ አብድልፈታ ናስር ጤናቸውን ለመጠበቅና የተሟላ ስብዕና ለመገንባት በአካል ብቃት እንቅስቃሴ በመርሀግብሩ ላይ መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ስፖርቱ በተለይ የእርስ በርስ ግንኙነታቸውን ከማጠናከር ባለፈ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን በጋራ ለማከናወን ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸውም ገልጸዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ ከተለያዩ መዋቅሮች የተውጣጡ ስፖርተኞችም መሳተፋቸው ታውቋል።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ አቮካዶን በኩታ ገጠም በማልማት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል
Jul 10, 2026 156
ደብረ ማርቆስ፤ ሃምሌ 3/2018(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን አቮካዶን በኩታ ገጠም በማልማት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ ገለጹ። ዋና አስተዳዳሪው እንደገለጹት ፤በዞኑ ደብረ ኤልያስ ወረዳ አቮካዶን በኩታ ገጠም በማልማት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ነው። ለዚህም የተሻሻለ ዝርያ ያላቸውን፣ በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡና በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸውን የአቮካዶ ችግኞችን በማዘጋጀት የችግኝ ተከላ ስራ ተጀምሯል ነው ያሉት። ዞኑ በሰብል ልማት ትርፍ አምራች ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ በመሆኑ አርሶ አደሩን በብዝሃ የአመራረት ስልት በማሳተፍ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ንጋቱ በበኩላቸው ፤በተያዘው ክረምት በደብረ ኤልያስ፣ ጎዛምንና ማቻከል ወረዳዎች የፍራፍሬ ልማትን በኩታ ገጠም የማካሄድ ስራ ተጀምሯል ብለዋል። በዛሬው እለትም በደብረ ኤሊያስ ወረዳ በአበሸም ቀበሌ አቮካዶን በኩታ ገጠም ለማልማት የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር መካሔዱን አስረድተዋል። በእለቱም በወረዳው ብቻ በ100 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም አቮካዶ ለማልማት የሚያስችል የችግኝ ተከላ መካሄዱን አብራርተዋል። በአጠቃላይ በዞኑ በኩታ ገጠም ለማልማት የሚያስችል ከ 917 ሺህ በላይ የአቮካዶ ችግኝ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱን አስረድተዋል። በምስራቅ ጎጃም ዞን በክረምቱ ከ 2 ሺህ 300 ሄክታር መሬት በላይ ፍራፍሬን በኩታ ገጠም ለማልማት የሚያስችል ከአንድ ነጥብ ሰባት ሚሊዮን በላይ ችግኝ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱም ተመልክቷል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን እያሳደገ ነው
Jul 9, 2026 680
ደብረ ብርሃን፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነዋሪዎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ የክረምቱን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በሲያደብርና ዋዩ ወረዳ "ጋራ መየ" ተፋሰስ ዛሬ አካሂዷል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደሰ ማሙሻ እንዳሉት ፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የለሙ ተፋሰሶች አርሶ አደሩ ከእለት ፍጆታው ያለፈ ምርት ለማምረት የሚያስችለውን አቅምን ፈጥሮለታል። በዋናነትም በመኖ ልማት፣ በእንስሳት እርባታና ማድለብ፣ በንብ ማነብ ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፎች እንዲሰማሩ ማስቻሉን ገልጸዋል። በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዞን ደረጃ በ36 ሺህ 284 ሄክታር መሬት ላይ ከ298 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ነው ያሉት። በዘንድሮው ዓመት የሚተከሉት ችግኞች የዞኑን የደን ሽፋን ከፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል። በክረምቱ ሁለት ነጥብ አራት ሚሊዮን የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በበኩላቸው ፤ህብረተሰቡ በየዓመቱ ችግኝ በመትከል ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጀመረውን ስራ አጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል ሲሉ አሳስበዋል ። የሚተከሉ ችግኞችም አሁን ያለውን አርሶ አደርና ወጣት ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር የመጪውን ትዉልድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የሲያ ደብርና ዋዩ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ደሱ ምክረ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሚተከሉ ችግኞች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸዉና ለአካባቢ ስነ ምህዳር ጥበቃ ከፍተኛ ፋይዳ የሚያበረክቱ ናቸው። በወረዳው በያዝነው ክረምት ስምንት ነጥብ አራት ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የሚያስችል የቦታ ዝግጅት ተካሂዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል። የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ዓለማየሁ ያዴቴ እንደገለጹት፤በዘንድሮው ዓመት ከዚህ በፊት ከተከሏቸው ችግኞች 30 ሺህ ብር ገቢ ማግኘታቸውን ጠቁመዋል ። የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የጽድቀት ምጣኔያቸውን ለማሳደግ እንሰራለን ሲሉም ገልጸዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይም ከዞንና ከወረዳ የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን በክረምቱ ወቅት በሁለት ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ልማት ይካሔዳል
Jul 9, 2026 373
ደብረ ማረቆስ ፤ሃምሌ 2/2018(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁለት ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍን የፍራፍሬ ልማት እንደሚካሔድ የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ። በመምሪያው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባለሙያ አቶ ተሾመ በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤በተያዘው ክረምት ለሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአንድ ሚሊዮን በላይ የፍራፍሬ ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል። ለተከላ ከተዘጋጁት ችግኞች ውስጥ የአቮካዶ፣ ብርቱካን ፣ ማንጎ ፣ ሎሚ ፣ ፓፓያ እና የአፕል ዝርያዎች እንደሚገኙበት ነው ያመለከቱት። የችግኝ ተከላው በሁለት ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የሚካሔድ ሲሆን እስካሁን በተደረገው ጥረት ከ80 ሺህ በላይ የፍራፍሬ ችግኝ መተከሉን ገልፀዋል ። በዚሁ የፍራፍሬ ችግኝ ተከላ ከ20 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን እንደሚሳተፉም ነው ያመለከቱት። በአሁኑ ወቅትም አርሶ አደሩ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በፍራፍሬ ልማት ተሳትፎ ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥ የተሻሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ለአብነትም ባለፉት ጥቂት ዓመታት ቡናን ጨምሮ ሌሎች የፍራፍሬ አይነቶችን በማልማት አርሶ አደሩ ቋሚ ገቢ በማግኘት ጥሪት እንዲያፈራ እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በየደረጃው ያለው የዘርፉ አመራርና በላሙያም አርሶ አደሩን በመደገፍ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት ጥቂት ዓመት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በፍራፍሬ ልማት መሸፈኑን ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በአቮካዶ ምርት የተመዘገበውን ስኬት በቆላ ፍራፍሬ ልማት ለመድገም እየተሰራ ነው
Jul 8, 2026 628
ገንዳ ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- የአቮካዶ ምርትን ወደ ውጭ በመላክ እየተመዘገበ ያለውን ስኬት በሌሎች የቆላ የፍራፍሬ ልማቶች ለመድገም የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በምዕራብ ጎንደር ዞን "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዞኑ በገንዳውኃ ጊዮርጊስ ተፋሰስ ተጀምሯል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊና ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንደገለጹት ፤ለዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ ችግኞች በማዘጋጀት የተከላ ስራ ተጀምሯል። ለተከላ የተዘጋጁት ችግኞችም ለምግብነት የሚውሉ፣ ቀጥተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የደን ዝርያዎችና ለእንስሳት መኖ የሚውሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዞኑ ለቆላ ፍራፍሬ ልማት ያለውን ምቹ የአየር ንብረት፣ ለም መሬትና ከፍተኛ የውሃ አማራጭ በመጠቀም የተሻለ ውጤት ለማምጣት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። "ለፍራፍሬ ልማት ቀደም ብለን ተዘጋጅተናል" ያሉት ኃላፊው ከ200 ሺህ በላይ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች በክላስተር መዘጋጀቱን ጠቁመው ከ600 ሺህ በላይ የሙዝ፣ ማንጎ ፣ ዘይቱን ፓፓያና ብርቱካን ችግኞች ይተከላሉ ብለዋል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በበኩላቸው “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የዞኑ ሕዝብ በንቃት በመሳተፍ ተጠቃሚነቱን እንዲያሳድግ አሳስበዋል። ችግኞችን ከመትከል ባለፈ፣ በዘላቂነት ፀድቀው ለታለመላቸው ፍሬ እንዲበቁ ተገቢውን እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባም ነው ያመለከቱት። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት ወጣት አሸናፊ ታፈረና ደጉ ገብረ እግዚአብሔር በበኩላቸው፣በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች በአጭር ጊዜ ለውጥ ማምጣታቸውን እንደተመለከቱ ተናግረዋል። እየተገኘ ያለውን ጥቅም ለማሳደግም በክረምቱ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ያለምንም ቀስቃሽ በፈቃዳቸው በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን አስረድተዋል። በማስጀመሪያው መርሐግብሩ ላይ የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች፣ የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 17816
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 11699
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 10496
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 10393
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
ላሊበላ፦ ከዓለም አቀፍ ቅርስነት እስከ ባህል ዲፕሎማሲ ማዕከልነት
Jul 9, 2026 567
በሙሴ መለሰ ከ40 በላይ ኤምባሲዎችን ጨምሮ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የተወከሉ ከ70 በላይ ከፍተኛ ዲፕሎማቶችና የልማት አጋሮች ከአፍሪካ እጅግ አስደናቂ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶች መገኛ በሆነችው በታሪካዊቷ የላሊበላ ከተማ ከሰሞኑ ጉብኝት አድርገዋል። ይህ ታሪካዊ ጉብኝት በዓለም አቀፍ ደረጃ የላሊበላን ውቅር አብያተ ክርስቲያናት የመንከባከብና የመጠበቅ የጋራ ቃልኪዳንን በድጋሚ ለማደስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ይህን ዲፕሎማሲያዊ ጉብኝት ያዘጋጀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ከቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን፣ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ ከአማራ ክልል መንግሥት፣ ከላሊበላ ከተማ አስተዳደር እና በፈረንሳይ መንግሥት ድጋፍ ከሚንቀሳቀሰው “ዘላቂ ላሊበላ” ፕሮጀክት (Sustainable Lalibela Project) ጋር በመሆን ነው። ላሊበላ እ.አ.አ በ1978 በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ መዝገብ ላይ የሰፈሩት ድንቅ አብያተ ክርስቲያናትን ይዛለች። ከስምንት መቶ ዓመታት በፊት (በ13ኛው ክፍለ ዘመን) ከአንድ ወጥ አለት ተፈልፍለው የታነጹት 11ዱ ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናት፤ ዛሬም ድረስ መላውን ዓለም በአድናቆት የሚጎበኛቸው፣ የጥንታዊ ምህንድስና እና የመንፈሳዊነት ጥልቅ መገለጫዎች መሆናቸውን ዩኔስኮ ጉብኝቱን አስመልክቶ ባወጣው ጽሁፍ ላይ አመልክቷል። በጉብኝቱ የተሳተፉት ዲፕሎማቶች እንደ ቤተ መድኃኔዓለም፣ ቤተ ማርያም፣ ቤተ ጊዮርጊስ፣ ቤተ አማኑኤል እና ቤተ ቅዱስ መርቆሬዎስ ያሉትን አብያተ ክርስትያናት ተመልክተዋል። ዲፕሎማቶቹ ላሊበላን “ከዚህ ዓለም ስሪት የላቀ እፁብ ድንቅ ጥበብ” ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ቅርሶቹ የጥንታውያኑን አባቶች ድንቅ የምህንድስና ጥበብና የስነ-ህንጻ ልህቀት ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ መሆናቸውን በአድናቆት ተናግረዋል። ዲፕሎማቶቹ ከአብያተ ክርስቲያናቱ ጉብኝት ባሻገር ከነዋሪው፣ ከአካባቢው ማህበረሰብ እና ከሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት አድርገዋል። ይህ ውይይት ልዑካኑ የላሊበላን ህያው ቅርስ ለመጠበቅ የሚደረጉ ጥረቶችን እና ይህንን ታሪካዊ ስፍራ ለቀጣዩ ትውልድ ለማቆየት እየገጠሙ ያሉ ወቅታዊ ተግዳሮቶችን መፍታት ስለሚቻልበት ሁኔታ በተሻለ መልኩ ለመረዳት አስችሏቸዋል። ጉብኝቱ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በቅርቡ በአካባቢው ከተከሰቱ ፈተናዎች በኋላ፣ የላሊበላን የቱሪዝም እንቅስቃሴ መልሶ ለማገገም እና ለማነቃቃት ትልቅ ዕድል ፈጥሯል። ጎብኚዎቹ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ባህል ሰዎችን በማቀራረብና የእርስ በርስ መግባባትን በማጠናከር ረገድ ስላለው የማይተካ ሚና አጽንኦት ሰጥተዋል። ዩኔስኮ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎ እና ከሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ለፈረንሳይ መንግሥት እና ለጉብኝቱ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናውን አቅርቧል። ጉብኝቱ የላሊበላን ባህላዊ፣ መንፈሳዊና ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶች እና እሴቶች ባሉበት ለተተኪው ትውልድ ለማሻገር ያለውን ዓለም አቀፍ ቁርጠኝነት ያረጋገጠ መሆኑን ድርጅቱ አመልክቷል። ዩኔስኮ በቅርሱ አያያዝ፣ ጥበቃ እና ቀጣይነት ላለው አስተዳደር ዙሪያ ከኢትዮጵያ መንግስት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ቴክኒካዊ ትብብር እና በአቅም ግንባታ ለበርካታ አስርት አመታት በቅርበት ሲሰራ መቆየቱንና የቅርሱን ዓለም አቀፍ ሀብትነት ጠብቆ ለማቆየት ይህንኑ ተግባሩ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በጽሁፉ አረጋግጧል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jul 5, 2026 1506
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018(ኢዜአ):- የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? ኢትዮጵያ እያከናወነች ነው የገጠር ትራንስፎርሜሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት የተጀመረው የከተሞች ኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩም ተስፋፍቶ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗርና አመጋገብ እንዲሁም ጤናን መሰረት በማድረግ የገጠር ኮሪደር ልማት በመከናወን ላይ ይገኛል። ለጤናም ይሁን ለኑሮ ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ለዘመናት በተመሳሳይ ሁኔታ የኖረው አርሶና አርብቶ አደሩ አሁን ላይ መሰረታዊ የአኗኗር ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በገጠር የኮሪደር ልማት የሰዎችና እንስሳት መኖሪያ እየተለየ፤ በባዮ ጋዝ እና በፀሃይ ብርሃን በሚሰራ የሃይል ምንጭ መብራት ማግኘትና ምግብ መስራት የተቻለበት፤ በጓሮ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎችን መመገብ የሚቻልበት ዘመናዊ አኗኗር ጀምረዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን የልማት እንቅስቃሴው በጅምር ላይ ቢሆንም በብዙ አካባቢዎች እየተስፋፋ ሞደል መንደሮች እየተበራከቱ መጥተዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ሀማሳ በ79 ነጥብ 4 ሄክታር መሬት ላይ የተሰራው ሞዴል መንደር የዚሁ ጥረት ማሳያ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቆ ለነዋሪዎች የተላለፈው የሀማሳ ሞዴል መንደር በአንድ ግቢ ውስጥ የንጽህና መጠበቂያ፣ የተደራጀ የቤት እንስሳት ማቆያ፣ በባዮ ጋዝ የሚሰራ የሃይል አቅርቦትን እንዲሁም የተሟላ የጓሮ ግብርናን ማእከል አድርጎ የተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም መንግሥት በተለያዩ የገጠር አካባቢዎች ሞዴል ቤቶችን መስራቱን አስታውሰው ከዚህ በመነሳት ነዋሪዎቹ በራሳቸው ተነሳሽነት የራሳቸውን መኖሪያዎች መገንባት ጀምረዋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው ''ንጽህና ካለ ጤና አለ፤ ምግብ ካለ ጤና አለ፤ የተስተካከለ ኮሪደር ካለ ሰላም አለ። እነዚህ ጉዳዮች ከፍተኛ ግምት ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል። የዜጎቻችንን ሕይወት ይቀይራሉ፤ የአኗኗር ዘዬአችንን ያሻሽላሉ፤ ኢትዮጵያን ወደ ምናስበው ከፍታ ወደ ምናስበው መሻሻል የመውሰድ አቅም አላቸው'' ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ቀጥሎ በጋሞ ዞን የ'ዮ ሆልዲንግ’ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከጥቂት ዓመታት በፊት ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚሆን የድንጋይ ከሰል ከውጭ ሀገር ለማስገባት እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር ውጪ የሚደረግ መሆኑን አንስተዋል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ የተለያዩ የከሰል ማምረቻ ፋብሪካዎች ተመርቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውንና ይህም የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ ለውጭ ገበያ የማቅረብ እድል ይፈጥራል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአርባምንጭ ዘመናዊ የኮንፈረንስ ሪዞርት መርቀው ስራ ያስጀመሩ ሲሆን በዶርዜ ሎጅ እና አካባቢው መሰረተ ልማቶችን እንዲሁም የአርባ ምንጭ ከተማን የኮሪደር ልማት፤ በከተማዋ የሚገኘውን ኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓንም ጎብኝተዋል። በሁሉም ዘርፎች ኢትዮጵያ ማከናወኗን አጠናክራ ቀጥላለች፤ እድገትና ማንሰራራቷ ላይቀለበስ ጉዞውን ቀጥሏል። ከዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች አንዱ የቱሪዝም ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት እንዳስታወቀው የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በዓለማችን ከፍተኛ ተጓዦች ከተመረጡ የዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች መካከል አንዱ ሆኗል። በዩሮኒውስ የዜና አውታር በተደረገ ጥናት፤ ሁሉንም የዓለም ክፍሎች ያዩ አንጋፋ ተጓዦች ካስቀመጧቸው ተወዳጅ የዩኔስኮ የዓለም ቅርሶች መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በግንባር ቀደምትነት ተቀምጧል። በዚሁ ሳምንትም ከአርባ በላይ ሀገራት እና ከአሥር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ዲፕሎማቶች የላሊበላ ከተማና ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። ይህ ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑክ በቆይታው ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን፣ የሕንጻ ጥበብ እና የኢንጂነሪንግ ጥበብ ማስተርፒስ እንዲሁም የሃይማኖትና የታሪክ ሕያው ምስክር የሆኑትን የዓለም ቅርስ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አስተማማኝ መከታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ያሰለጠናቸውን ተመራቂዎች በዚሁ ሳምንት አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ሰራዊቱ የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝ መልኩ እየጠበቀ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ ታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች ግንባር ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያን ከባሕር ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ “ፅምዶ” በሚል የተሰለፉ አካላት ስለመኖራቸው ተናግረዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአደረጃጀት ልዩ እና በዘመናዊ ትጥቅ ተጠናክሮ በማንኛውም ሁኔታ ለሀገሩ ክብርና ሉአላዊነት መጠበቅ አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል። የ12ኛ ክፍል ፈተና በሳምንቱ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ስኬታማ በሆነ መልኩ ተከናውኗል። በሁሉም አካባቢዎች ተፈታኞች በበይነመረብ (ኦንላይን) እንዲሁም በወረቀት እንደየ ዝግጅቱና ምቹ ሁኔታውን መሰረት በማድረግ ፈተናውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በገጠር ኮሪደር አዲስ የህይወት ምእራፍ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የጊምቦ ወረዳ በተገነባው ሞዴል የገጠር መንደር የሚኖሩ አርሶ አደሮች አዲስ የህይወት ምእራፍ መጀመራቸውን ገልጸዋል። የኤሌክትሪክና ሌሎች አገልግሎቶች የተሟላለት የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር የአኗኗር ዘይቤያችንን ምቹና ዘመናዊ አድርጎታል ያሉት ነዋሪዎቹ ይህንን ላደረጉ ሁሉ እናመሰግናለን ብለዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ የተገነባውን የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የግብርናና ገጠር ሽግግርን እውን በማድረግ የአርሶ አደሩን አኗኗር ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ገልፀው የመብራት፣ የውሃ፣ የመንገድን ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን አርሶ አደሩ በአቅራቢያው ማግኘት የሚያስችልና የኢኮኖሚ አቅሙን የሚያሳድጉ መሆናቸውን በወቅቱ ተናግረዋል። በቀጣይም ተግባሩን በማስፋት ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግን ፍልሰት ለማስቀረት በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ አኔ ዲማ ወረዳ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰኣዳ አብዱረህማንና የከተማው ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎችም የአከባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰዓዳ አብዱረህማን በወቅቱ፤ ዛሬ የምንተክላቸው ችግኞች ለሀገራችን ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ የሚሰጡ ናቸው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለትውልድ ቀጣይነት አስተማማኝ ዋስትና ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)፤ በሸገር ከተማ የአካባቢውን አረንጓዴነት ለማረጋገጥና ኢኮኖሚውን ለመደገፍ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን የተለያዩ ዝርያ ያላቸውና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር ገብተናልም ብለዋል። የባቡር መስመር ጥገና የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በቅርቡ የጥገና ስራው የተጀመረውን የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ የባቡር መስመር ፕሮጀክት የጥገና ሂደት በዚሁ ሳምንት ጎብኝተዋል። ከአዋሽ -ኮምቦልቻ -ሃራ ገበያ 392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን ፕሮጀክት በአራት አቅጣጫ የጥገና ሥራው እየተከናወነ መሆኑም ታውቋል። ለልማት ተነሽዎች የተገነቡ ቤቶች በዚሁ ሳምንት የጅማ ከተማ አስተዳደር ለልማት ተነሺዎች ያስገነባውን 300 መኖሪያ ቤቶች መርቆ ማስረከቡን እንመለከታለን። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ፤ በክልሉ በገጠርም ይሁን በከተሞች ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሃ ቀመር፤ በከተማው በርካታ ፕሮጀክቶች በመንግስት እየተከናወኑ እንደሆኑና የተጠናቀቁትም ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በከተማዋ በዚህ አመት 80 የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ጠቅሰው ዛሬ ለልማት ተነሺዎች ተገንብተው የተላለፉ መኖሪያ ቤቶች የዚሁ ጥረት አንድ አካል ናቸው ብለዋል። እነዚህ መኖሪያ ቤቶች ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው ግንባታቸው ተጠናቆ ለ300 አባወራና እማወራዎች ተላልፈዋል ብለዋል።
ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች
Jun 29, 2026 4012
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • ምንድንነት የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም ‘አስም’ እንደሚባልም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የኪንታሮት ህመም እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? • ምልክቶች የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ጠቁመዋል። ምልክቶቹም በአብዛኛው በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ አስገንዝበዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር)፣ የእንስሳት አይነ ምድር ሽታዎች ለዚህኛው አስም አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን አስረድተዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑንም ተናግረዋል። • አጋላጭ (ለህመሙ መባባስ) መንስዔዎች አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የዓየር ብክለት፣ ጭስ)፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ዓይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? 👉ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎችዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ 👉 በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ 👉 በቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ ሙቀት የሚሰጡ መከላከያ ልብሶችን መልበስ፤ 👉 ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ • ሕክምናው የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የዓየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ከ 3 እስከ 10 በመቶ ያህሉ የዓለም ሕዝብ በአስም ተጠቂ መሆኑንም ጠቁመዋል። #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢዜአ #የጤና_ነገር
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 3738
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ትንታኔዎች
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 2308
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 2258
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 2298
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 6028
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 8539
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 19677
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 12727
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 18476
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 4734
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 3437
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።