ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ሞሮኮ ካናዳን 3ለ0 በመርታት በዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆነች
Jul 4, 2026 112
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ሞሮኮ ካናዳን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በሂውስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የ26 ዓመቱ የአማካይ ተጫዋች አዜዲን ኡናሂ በ50ኛው ፤ በ82ኛው እና ሶፊያን ራሒሚ በጭማሪ ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥሯል። የሰሜን አፍሪካዋ ሞሮኮ በመጀመሪያው አጋማሽ ብልጫ ቢወሰድባትም በሁለተኛው 45 የተሻለ እንቅስቃሴ አድርጋለች። የሞሮኮው ወሳኝ ተጫዋች ኢስማኤል ሳይባሪ (አጥቂ) ባጋጠመው የጡንቻ ጉዳት ምክንያት በ22ኛው ደቂቃ በሶፊያን ራሂሚ ተቀይሮ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ሞሮኮ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለች የመጀመሪያ ሀገር ሆናለች። በሩብ ፍጻሜው ከፓራጓይ እና ፈረንሳይ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ኳታር እ.አ.አ በ2022 በተካሄደው 22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮ ግማሽ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያ አፍሪካዊ ሀገር በመሆን ታሪክ መስራቷ ይታወቃል። የአትላስ አንበሶች በዘንድሮውም የዓለም ዋንጫ በስኬታማ ጉዟቸው ቀጥለዋል። ከዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ካናዳ ጉዞዋ 16 ውስጥ ተገቷል። በሌላኛው የ16ቱ ጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ፓራጓይ ከፈረንሳይ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ላይ በፊላደልፊያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው
Jul 4, 2026 141
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለፁ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፣ የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት፤ የሲዳማ ክልል የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ባለሀብቶች ወደ ሀዋሳ በመምጣት እውቀትና ሀብታቸውን ተጠቅመው በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል። ሀዋሳ መተላለፊያና ማረፊያ ከተማ በመሆኗ ባለሃብቶች በአካባቢው ያለውን ዕድል እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል። ሀዋሳን በጋራ ለመገንባት የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው በቁርጠኝነት ለሰሩና የበኩላቸውን ሚና ለተወጡም ምስጋና አቅርበዋል። ሀዋሳ የደቡብ ፈርጥ፣ የሰላም ደሴት፣ ባላት ውብ ተፈጥሮ ምድረ ገነት የተባለች፣ እንዲሁም የህዝቡ እንግዳ ተቀባይነት የፍቅር ቤት ያስባላት ከተማ መሆኗን አንስተዋል። ሀዋሳን ለኑሮ፣ ለመዝናኛ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት የተመቸች ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው፣ የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ የፕሮጀክት መገንቢያ ብቻ ሳይሆን፣ የነገንና አዲሱን ምዕራፍ በጋራ ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ሀዋሳ በተፈጥሮ የታደለች ናት ያሉት ከንቲባው፤ ከተማዋን አልምቶ ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የሀዋሳ ሐይቅ የቱሪዝም ምንጭና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን አንስተው፤ የሐይቁን ዳርቻ ማልማት የከተማዋን ገጽታና ተስፋ የሚቀይር ታሪካዊ ስራ መሆኑንም ገልጸዋል። ሀዋሳን ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለቱሪዝም ምቹ እንዲሁም ከተማዋን የአፍሪካ የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የፍቅር ሐይቅ፣ አሞራ ገደልና ዓሳ ገበያን ለነዋሪዎቿና ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ መታቀዱንም ተናግረዋል። ከተማዋን በዘመናዊ መንገድ ለመገንባት ለተወጠነው ፕሮጀክት ከሦስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ በጀት እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ከዚህ መካከል ሁለት ቢሊዮን ብር ከከተማ አስተዳደሩ፣ አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብሩን በገቢ ማሰባሰቢያ ለማግኘት መታቀዱን አስረድተዋል። ባለፉት ሁለት ወራት በቀረበው ጥሪ መሰረት በመጀመሪያው ዙር የሀብት ማሰባሰቢያ ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው፤ የዛሬው መድረክም የመጀመሪያ ዙር የሀብት ማሰባሰቢያ ማጠናቀቂያ መሆኑን ተናግረዋል። የሀዋሳ ሐይቅን ለማልማት የከተማዋ ነዋሪዎች፣ ባለሃብቶችና ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የድህነትና ኋላቀርነት ታሪክን በሚሰብር የመነሳትና የብልፅግና የእጥፋት ዘመን ላይ ናት
Jul 4, 2026 129
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የድህነትና ኋላቀርነት ታሪክን በሚሰብር የመነሳትና የብልፅግና የእጥፋት ዘመን ላይ ናት ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ ሀገራት ከችግርና ጉስቁልና የሚሻገሩበት የእጥፋት ጊዜ አለ። ኢትዮጵያ ያለችበት ዘመን የእጥፋት፣ ብልፅግናና የመነሳት ዘመን መሆኑንም ተናግረዋል። በአዲስ አበባ በመንግስት መሪነት፣ በግል ባለሀብቱ ተሳትፎና ትብብር የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የሀዋሳ የልማት ፕሮጀክት ትልቅ በጀት የሚጠይቅ፤ ሲጠናቀቅም ለነገ ተጠቃሚነት ማረጋገጫ መሆኑንም ጠቁመዋል። በሁሉም አካባቢዎች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። አንድነታችንን እንደጋሻና ጦር በመጠቀም ኢትዮጵያን ከድህነትና ኋላቀርነት የምናላቅቅበትና በጋራ የምናለማበት መጪው ጊዜ ብሩህ ነው ብለዋል። መድረኩ ብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ይሁንታ አግኝቶ በተመረጠበትና ለመንግስት ምስረታ እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት መዘጋጀቱ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው ነው ብለዋል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን በመኸር እርሻ ከ485 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም ይለማል
Jul 4, 2026 177
ደብረ ማርቆስ ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ጎጃም ዞን በመጭው የመኸር ምርት ዘመን ከ485 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እርሻ እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ እንቢአለ አለኽኝ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ከ669 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥ ከ485 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በኩታ ገጠም እንደሚለማ ነው የተናገሩት። በመኸር እርሻ የምርት ማሳደጊያ ግብአት ፣ ቴክኖሎጂና አዳዲስ አሰራሮችን በተሻለ መንገድ ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም አርሶ አደሩ ከራሱ አልፎ ለገበያ የሚያቀርበው ትርፍ ምርት ለማምረት እንደሚችልም ነው የተናገሩት። ከ100 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የስንዴ፣ ጤፍ ፣ ማሽላ ፣ የቢራ ገብስ ፣ በቆሎና ቦለቄ ሰብሎችን በኩታ ገጠም ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን በተደረገው ጥረትም ክረምቱ ቀድሞ በገባባቸው አካባቢዎች ከ90 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን ተናግረዋል። በኩታ ገጠም ልማቱ ከ20 በላይ ትራክተሮች በእርሻ ስራው ላይ መሰማራታቸውን ጠቁመው ይሕም የአርሶ አደሩን ጊዜ፣ ገንዘብና ጉልበት በመቆጠብ በሌሎች የልማት ስራዎች እንዲሰማራ የሚያደርግ ነው ብለዋል። እስካሁን በኩታ ገጠም በዘር ለተሸፈነው መሬትም ከ250 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን ይህም ምርታማነትን በማሳደግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያግዝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዞኑ የደብረኤሊያስ ወረዳ የገነቴ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አየነው በቀለ እንደገለጹት፤አንድ ሄክታር መሬታቸውን በኩታ ገጠም በማልማት በቆሎ መዝራታቸውን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመትም በኩታ ገጠም ካለሙት ስንዴና በቆሎ ያገኙትን ተጨማሪ ምርት ለገበያ በማቅረብ የኢኮኖሚ አቅማቸውን ማሳደጋቸውን አስረድተዋል። የደጀን ወረዳ የኩራር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ያደለው በዛ በበኩላቸው፤ ባለፈው የምርት ዘመን ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በኩታ ገጠም ማሽላ በመዝራት ተጨማሪ የአራት ኩንታል ምርት እንዳገኙ ነው የሚገልጹት። በዘንድሮ ዓመትም ተጠቃሚነታቸውን ለማስፋት በአካባቢው ካሉ አርሶ አደሮች ጋር በጋራ በመሆን በኩታ ገጠም ማሽላን መዝራታቸውን አብራርተዋል። የኩታ ገጠም አሰራር ዘርንና ግብአት አጠቃቀምን በተመሳሳይ ጊዜ ከማካሄድ ባሻገር የሚዛመት የሰብል በሽታን፣ አረምንና ተባይን በጋራ ለመከላከል የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል። በዞኑ በመኸር ምርት በአጠቃላይ ከሚለማው ከ669 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ከ26 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት መታቀዱንም ነው ያመለከቱት።
በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች ከአካባቢው ጸጋ እና ከኢንዱስትሪ ፍላጎት ጋር መጣጣም ይጠበቅባቸዋል
Jul 4, 2026 165
ወልቂጤ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚሰጧቸው ስልጠናዎች ከአካባቢ ፀጋ እና ከኢንዱስትሪው ፍላጎት ጋር መጣጣም እንዳለባቸው የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ የስልጠና መስክ ልየታ ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና በወልቂጤ ከተማ ሰጥቷል፡፡ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር ሰለሞን ፈርሻ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አዲሱ የስልጠና ልየታ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ገበያው እና ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን የሰው ኃይል ማፍራት ላይ እንዲያተኩሩ የሚያስችል ነው። በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ ተመስርተው የልህቀት ማዕከል በመሆን ዘመኑን የዋጀ እውቀትን ማስረጽ ላይ አተኩረው መስራት እንዳለባቸውም ተናግረዋል። የአካባቢውን የልማት እንቅስቃሴ እና ጸጋ መጠቀም የሚችል የሰለጠነ ብቁ የሰው ሃይል በማፍራት የሰልጣኞችን ተመራጭነትና ተወዳዳሪነት ማሳደግ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የክልሉ ፖሊሲ ጥናት እና ምርምር ኢንስቲትዩት ተመራማሪ አበራ ኤልያስ (ዶ/ር) ፤ ኮሌጆች በአካባቢያዊ ፀጋ እና በሥራ ገበያ ፍላጎት መሰረት ወቅቱን የዋጀ ሙያ ላይ አተኩረው እንዲሰሩ ጥናት ተደርጓል ብለዋል። ይህም ሰልጣኞች የተሻለ ክህሎትና እውቀት ይዘው ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፣ ይህም ተቋማቱ ተወዳዳሪ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት ያስችላቸዋል ብለዋል። የወራቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አካዳሚክ ዘርፍ ምክትል ዲን ወይዘሮ ሶፍያ ዋበላ በበኩላቸው፤ አዲሱ የትምህርት ስልጠናና ስትራቴጂ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ ለትምህርትና ስልጠና ጥራት መረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። ስትራቴጂው በኢንዱስትሪ እና በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችና ወቅታዊ ሁኔታዎችን ባገናዘበ መንገድ በገበያው ተወዳዳሪ የሚሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል መሆኑንም አስረድተዋል። በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስኮች ልየታ አምራች፣ ግብርና፣ ቱሪዝም እና አገልግሎት ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ የስልጠና መስኮች የአካባቢ እና የሃገር እድገት ፍላጎትን መሰረት ያደረገ መሆኑ ለዘርፉ ውጤታማነት ወሳኝ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መምሪያ ሃላፊ አቶ አህመዲን ጀማል ተናግረዋል። የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የኢንዱስትሪውን ፍላጎት የሚያሟላ ብቃት ያለው የሰው ሀይል በተግባር እና በንድፈ-ሃሳብ ትምህርት ታግዘው እንዲያሰለጥኑ የሚያስችላቸው መሆኑንም ተናግረዋል። በመድረኩ የክልሉ የዘርፉ አመራሮችን ጨምሮ የዞንና የልዩ ወረዳ የቴክኒክና ሙያ መምሪያ ሃላፊዎች፣ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲኖች እና የዘርፉ አጥኚዎች ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
መከላከያ ሠራዊት የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት እየጠበቀ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Jul 4, 2026 680
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝነት እየጠበቀ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተመራቂዎች አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላምና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር)፣ የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ጥላሁን ደምሴ እና ከፍተኛ ጄኔራል መኮንኖች ተገኝተዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሥነ-ስርዓቱ ባስተላለፉት፤ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ የደህንነት ሁኔታ ውስብስብና ኢ-ተገማችነትን ታሳቢ ያደረገ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ የታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች የሴራ ጥምረት ወይም "ፅምዶ" ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊ ሰላምና ደህንነት በመጠበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለዘመናት በሰላም እጦት የሚገለፀው የቀይ ባሕርና አፍሪካ ቀንድ አከባቢ የደህንነት ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ እየተወሳሰበ መምጣቱን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው የምትገኝ፣ ከማንኛውም የቀጣናው ችግርና ተጠቃሚነት ማምለጥ የማትችል ትልቅ ሀገር መሆኗንም አስገንዝበዋል። ታሪካዊ ጠላቶችም ኢትዮጵያ ቀጣናውን የማረጋጋት የመሪነት ሚና እንዳትወጣና በውስጥ ጉዳዮች ብቻ እንድትጠመድ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በሌላ በኩልም ጎረቤቶችን እንዲታመሱ በማድረግ ለውስጣዊ ደህንነታችን ጫና መፍጠር የሚችሉ ሴራዎችን በመሸረብ ቀጣናውን ለማተራመስ አበክረው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ከባሕር ዳርቻ ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ ፅምዶ በሚል ስያሜ ዕድሳት ተደርጐለት እየተስተጋባ ነው ብለዋል። የዘመኑ ጦርነት በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በረጅም ርቀት ሚሳኤሎች፣ በሰው አልባ መሣሪያዎችና በሳይበር ኦፕሬሽኖች የታገዘ የቴክኖሎጂ ጦርነት መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም አደረጃጀቱንና ዘመናዊ ትጥቁን በማጠናከር በማንኛውም አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ቁመና ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ተመራቂዎችም የቀሰሙትን ስትራቴጂክ ዕውቀት ለሠራዊቱ ተጨማሪ ግንባታ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አሳስበዋል። የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ጥላሁን ደምሴ በበኩላቸው፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት የተመሰረተው ኮሌጁ በተለዋዋጭ ስትራቴጂክ ምህዳር ውስጥ የብሔራዊ ኃይል ማስፈፀሚያ አቅሞችን ውጤታማ ለማድረግ እየሰራ ነው ብለዋል። ኮሌጁ የስርዓተ ትምህርት ማሻሻያ በማድረግ በጥናት፣ ምርምርና የደህንነት ትንተና ላይ ትኩረት አድርጎ የአመራር አቅም ግንባታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል። መንግሥት የኮሌጁን የመሰረተ ልማትና የዲጂታላይዜሽን አቅም በማሳደግ ወደ ስማርት ኮሌጅ ለመቀየር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የአስተዳደሩ ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት ተገኝቷል
Jul 3, 2026 1157
ድሬደዋ፤ ሰኔ 26/2018(ኢዜአ)፦) የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የአስፈጻሚውን አካላት ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት መገኘቱን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አፈጉባኤ አብዲ ሙክታር ገለጹ። ምክር ቤቱ የስራ ዘመኑን መደበኛ ጉባኤ የፊታችን ሰኞ ያካሂዳል። የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር፣ ምክር ቤቱ የአስፈፃሚውን አካላት የአምስት አመታት የስራ እቅድና አፈጻጸም የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን አስመልክተው ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴዎቹና በሚቀርቡ ሪፖርቶች የተቀናጀ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ውጤታማ ስራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል ብለዋል። በሌላ በኩል የፍርድ ቤቶችን የአደረጃጀት፣ የበጀት እና በዳኞች ሹመት ላይ ቁጥጥር በማድረግም ለፍትህ ስርአቱ ስኬት የበኩሉን መወጣቱን አንስተዋል። ምክር ቤቱ አስፈጻሚው አካል የህዝብን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የወጡ ህጎችና ደንቦች ከህገ መንግስቱ ጋር በተናበበ መልኩ ስራ ላይ መዋሉን ሲከታተል መቆየቱን አንስተዋል። የኢኮኖሚ ዘርፎች በተቀናጀ መንገድ እንዲተገበሩ ድጋፍ በማድረግም ለውጤቱም የድርሻውን ማበርከቱን አንስተዋል። በመጪው ሰኞ በሚካሄደው በ3ኛው የስራ ዘመን 5ኛው አመት 12ኛው መደበኛ ጉባኤውም የአስፈጻሚውንና የምክር ቤቱ ተጠሪ ተቋማትን የ2018 በጀት አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ይገመግማል ብለዋል። በተጨማሪ የ2019 በጀት አመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።
በምክር ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች የውክልና ተሳትፎ ማደግ በሃሳብ ክርክር ላይ የተመሰረተ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ወሳኝ ነው
Jul 3, 2026 1027
አሶሳ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፡- በምክር ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች የውክልና ተሳትፎ ማደግ በሃሳብ ክርክር ላይ የተመሰረተ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ላለፉት በርካታ ዓመታት በአንድ ገዥ ፓርቲ ፍጹም ቁጥጥር ስር የነበረና የተፎካካሪ ፓርቲዎች ሚና እጅግ የተገደበ የነበረበት መሆኑ ይታወቃል። በሀገሪቱ የመጣውን የፖለቲካ ለውጥ ተከትሎ በተካሄዱት ጠቅላላ ምርጫዎች ግን፣ የምርጫ ሥርዓቱን ነጻ፣ ገለልተኛና ታማኝ ለማድረግ በርካታ የህግና የተቋማት ማሻሻያዎች ተደርገዋል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም ቀደም ባሉት ምርጫዎች የነበረው የተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎና የህዝብ ውክልና ዝቅተኛ የነበረ ቢሆንም፣ በሂደት በተደረጉ የፖለቲካ ሪፎርሞችና የውይይት መድረኮች ፓርቲዎች በነጻነት የመንቀሳቀስና አማራጭ ሃሳቦቻቸውን ለህዝብ የማቅረብ ዕድላቸው እያደገ መጥቷል። ይህ ውጤት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ የህዝብ ድምፅ አግኝተው የፖለቲካ ሥልጣን መጋራትና አማራጭ ሃሳብን ማሰማት የሚችሉበት ምህዳር እየተፈጠረ መሆኑን አመላካች ነው ተብሏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም የብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በመያዝ ያሸነፈ ሲሆን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም ከበፊቱ የተሻለ የክልል ምክርቤት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ አግኝተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንደተናገሩት፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳር እያደገ መምጣቱ የታየበት ነው። የቤኒሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ቤሕነን/ ፓርቲ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የነበረው የፖለቲካ ተሳትፎ ሀሳብ ብቻ ገዢ እና አሸናፊ የሆነበት ነው ብለዋል። ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ አካታች የሆነ የፖለቲካ ትርክትን መከተል እንደሚያስፈልግ ገልፀው፥ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በሁሉም መስክ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በቀጣይ በአሸናፊው የብልጽግና ፓርቲ የሚመሠረተው መንግሥት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ታሳቢ ማድረግ እንዳለበትና ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከመንግስት ጋር አብረው ለመስራት ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባም ጠቁመዋል። ይህም የፖለቲካ ፓርቲዎችን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር እና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እንዲዳብር የሚያግዝ ነው ብለዋል። ፓርቲያቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች ማግኘቱን የተናገሩት አቶ አብዱሰላም፤ ከክልሉ መንግስት ጋር የጀመሩትን ትብብር በማጠናከር ለክልሉ ሰላምና ልማት በጋራ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጉሕዴን) ማዕከላዊ ኮሚቴ ፀሐፊ አቶ ለሜሳ ኔኖ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባገኘው መቀመጫ ከመንግሥት ጋር የበለጠ ተቀራርቦ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም የሁሉንም ህዝብ ድምጽ በመስማትና የበለጠ ሀገራዊ ሀላፊነት እንደተረከበ ከግምት ውስጥ በማስገባት በሙሉ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል።
በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችሉ ናቸው
Jul 3, 2026 990
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው አሳታፊና አካታች ዐበይት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን በስልጡን የምክክር መፍትሔ ለመስጠት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሰናድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ከሚቀጥለው ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሂደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤም ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። በአጀንዳዎቹም የሀገር ግንባታ፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደርና ሰላም ግንባታ ናቸው። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉትም፤ የሀገራዊ ምክክሩ ስምንት የዋናው ጉባኤ የምክክር ዐበይት አጀንዳዎች የኢትዮጵያን ወሳኝ ጉዳዮች የያዙ ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩም በዜጎች መካከል ለዘመናት የሚነሱ የአለመግባባት ሃሳቦችን በምክክር በመፍታት በሁሉም መስክ የጋራ የፖለቲካል ኢኮኖሚ አቅም መገንባት እንደሚያስችል ገልጸዋል። አስተያየት ሰጪዎች መካከል መቶ አለቃ ጋዲሳ አብዲ፤ የሀገራዊ ምክክሩ የህዝብ አሳታፊና አካታችነት በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን ለመገንባት ወሳኝ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። የዋናው ጉባኤ ቁልፍ አጀንዳዎችም የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት በማስቀጠል በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያስችሉ ገልጸዋል። ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ገዛኸኝ ደሜ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ የዘመናት ቅራኔን በውይይትና ስምምነት መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ስምንቱ ዐበይት አጀንዳዎችም የህዝብን ፍላጎቶችና ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ማሸጋገር እንደሚያስችሉ ተናግረዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የህዝብ ተሳትፎና አካታችነት በመሰረታዊ የልማትና ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ መግባባትን በመፍጠር የጋራ ዕድገትን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ለማ ወተሬ ናቸው። በዋናው የምክክር ጉባኤ የሚመክሩ የህዝብ ወኪሎችም ስልጡን ምክክር በማድረግ ለሀገርና ህዝብ የሚጠቅሙ መፍትሔዎችን ማፍለቅ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ወጣት ክብሬ አባረዳ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር በጋራ አስተሳሰብና ፍላጎት የምትገነባ ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ መሰረት ይጥላል ብሏል። በዐበይት አጀንዳነት የሚመከርባቸው ጉዳዮችም ከህዝብ የመነጩና ለሀገራዊ ዕድገትና ሰላም መግባባትን ለመገንባት የሚበጁ መሆናቸውን ገልጿል።
የምክክር አጀንዳዎቹ የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና ጠንካራ አንድነትን ለመፍጠር ወሳኝ ናቸው
Jul 3, 2026 954
ቦንጋ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ):-ለዋናው የምክክር ጉባኤ የተለዩ አጀንዳዎች የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና ጠንካራ ሀገራዊ አንድነትና መግባባትን ለመፍጠር ሚናቸው የላቀ መሆኑን የቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ መምህራን ገለፁ። በሀገሪቱ ዘመናትን ያስቆጠሩ አለመግባባቶች በውይይት ለመፍታት ቁልፍ መሳሪያ የሆነው ሀገራዊ ምክክር በርካታ ሂደቶችን አልፎ ወደመቋጫው ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓም በሚያካሂደው ዋናው የምክክር ጉባኤም ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ለይቶ ይፋ አድርጓል። ተደራጅተው በቀረቡ የምክክር አጀንዳዎች ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ ምሁራን በኮሚሽኑ የተለዩ አጀንዳዎች ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ዋና ዋና ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ጠንካራ ሀገራዊ አንድነትና መግባባትን ለመፍጠር ጉልህ ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኮሌጁ የስነዜጋ እና ስነምግባር ትምህርት ክፍል መምህር እንግዳ ገብረማርያም እንደገለጹት፣ ችግሮችን በውይይትና በምክክር መፍታት የስልጣኔ መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሸን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ያሰባሰባቸውና አደራጅቶ ያቀረባቸው የምክክር አጀንዳዎች ልዩነቶችን ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የሚያስችሉ ናቸው። ይህም ለዘመናት ለቅራኔ ምንጭ የነበሩና የማያግባቡ ችግሮች በመፍታት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የተለያዩ ሂደቶችን አልፎ የሁሉንም አካባቢዎችና የህብረተሰብ ክፍሎች የሚወክሉ አጀንዳዎችን ለይቶ ማቅረቡ የሚደነቅ መሆኑን ያነሱት መምህር እንግዳ፣ ብዙ ውጣውረዶችን ያለፈው ምክክር ስኬታማ እንዲሆን የሁሉም አስተዋጾ ያስፈልጋል ብለዋል። በኮሌጁ የጂኦግራፊና የአካባቢ ጥናት ትምህርት ክፍል መምህር አለማው ብሩ በበኩላቸው፣ አለመግባባቶችን በውይይት መፍታትን ባህል ማድረግ ለጠንካራ ሀገረ መንግት ግንባታ ሁነኛ መሳሪያ መሆኑን አንስተዋል። እንደሀገር ባለፉት ዘመናት የተፈጠሩ ልዩነቶችን በውይይትና በምክክር ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ብዙ ሂደቶችን አልፎ ወደመቋጫ ምዕራፍ ላይ መድረሱን አድንቀው፣ ምክክሩ የሚፈለገውን ውጤት እንዲያመጣ ታሪካዊ ዕድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባናል ብለዋል። ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የነቃ ተሳትፎ በማድረግና ይህን ወርቃማ ዕድል ወደውጤት መቀየር አስፈላጊ መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል። የሀገረ መንግስት ግንባታ፣ የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርአት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሂደት፣ የፌደራል ከተሞች (አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ የሐይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነት ለዋናው ጉባኤ ከተለዩ አጀንዳዎች መካከል ይገኙበታል። በተጨማሪም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች፣ ሙስና እና መልካም አስተዳደር፣ ሰብአዊ መብቶች፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እንዲሁም የሰላም ግንባታ ጉዳዮች ምክክር የሚደረግባቸው ነጥቦች መሆናቸውም መገለጹ ይታወሳል።
የሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የኢትዮጵያን የተስፋ ጉዞ የሚወስን ልዩ የታሪክ ምዕራፍ ነው - ምሁራን
Jul 3, 2026 1157
አዲስ አበባ ፤ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የኢትዮጵያን የተስፋ ጉዞ የሚወስን ልዩ የታሪክ ምዕራፍ ነው ሲሉ አንጋፋ ምሁራን ገለጹ፡፡ ዜጎች ለምክክሩ ስኬታማነት እስካሁን ያሳዩትን የነቃ ተሳትፎ ማጠናክር እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰኔ 17 ቀን 2018 ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ የተለያዩ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ይፋ አድርጓል፡፡ እነኚህም ዋና ዋና የጉባኤው አጀንዳዎችም የሀገር ግንባታ፤ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት፤ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ፤ የሃይማኖት ጉዳዮች፤ የተቋማት ግንባታ፤ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፤ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፤ ሙስናና መልካም አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ናቸው፡፡ በእነኚህ ዋና ዋና አጀንዳዎች ዙሪያም ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ በሚጀምረው ጉባኤ ምክክር ይካሄድባቸዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክሩ የእስካሁኑ ጉዞ፤ እውነተኛ አሳታፊነትን፣ ፍፁም ግልጽነትን እና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በማካተት ስራዎችን በስኬት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የታሪክ ኤምሬተስ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ሀገራዊ ምክክሩ ስር የሰደዱ ችግሮች የሚፈቱበት አማራጭ የሌለው ሂደት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን ከሚያራርቃቸው ጉዳዮች ይልቅ የሚያቀራርቧቸው እንደሚበልጡ ነው የጠቆሙት፡፡ ይህም ምክክሩ ችግሮችን በሰከነ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ልዩ የታሪክ አጋጣሚ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አማካሪ ፕሮፌሰር አድማሱ ገበየሁ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክሩ በመመካከርና በመነጋገር የጋራ ግንዛቤ የሚፈጠርበት ትልቅ መድረክ ነው። ይህ ሂደት ኢትዮጵያን በተሟላ ሁኔታ ተጠቃሚ እንደሚያደርግና ምክክሮቹም ወደ ሀገራዊ መግባባት የሚወስዱ ናቸው ብለዋል፡፡ የምክክር ኮሚሽኑ እስካሁን የተጓዘበት ሂደት የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም የህዝብ ተሳትፎን ከማረጋገጥ አኳያ የተመዘገበው ስኬት በሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ታይቶ የማይታወቅ መሆኑን ገልጸዋል። የፖለቲካል ሳይንስ ተመራማሪና የህግ ጠበቃው ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል እየተቀየረ ለመምጣቱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክክሩ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት እንዳይግባቡ ያደረጓቸውን መሠረታዊ ችግሮች ራሳቸው መፍትሄ እንዲያስቀምጡላቸው በር የሚከፍት መሆኑን ጠቁመዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያዊያን ስር የሰደዱ ችግሮችን በጥልቀት መመካከር አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሄዎችን ለማምጣት ሁነኛ መንገድ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ለምክክሩ መሳካት ወጣቶችና ምሁራን እንዲሁም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በባለቤትነትና በሃላፊነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ጠቅሰዋል፡፡
የኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት ግንኙነት በሁሉም መስክ ወደ ላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው - አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር
Jul 2, 2026 1987
አዲስ አበባ፣ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት ግንኙነት በሁሉም መስክ ወደ ላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ገለጹ። አምባሳደር ሶፊ ኢመስበርገር ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት ታሪካዊ ግንኙነት ስኬታማ የትብብር ዕድገት እያስመዘገበ ነው። ለአብነትም ከወራት በፊት የኢትዮ-አውሮፓ የንግድ ፎረም በርካታ የኢትዮጵያና የአውሮፓ ኩባንያዎች በተሳተፉበት በፈረንሳይ ፓሪስና በአዲስ አበባ መካሄዱን አስረድተዋል። ፎረሙ የኢትዮ-አውሮፓን የኢኮኖሚ ግንኙነት ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን ወደ አውሮፓ ለመጓዝ የቪዛ ማመልከቻቸውን ከ45 ቀናት በፊት ማስገባት እንዳለባቸው የሚደነግገው የቪዛ ገደብ መነሳቱም የንግድና የባህል ግንኙነትን እያጠናከረ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት፣ ዲጂታላይዜሽን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪና የጤና ጥበቃ ስኬቶችም ከአውሮፓ ሕብረት የልማት መርሃ ግብር ጋር በእጅጉ የሚጣጣም መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም በኢትዮጵያ የሚደረጉ የመሰረተ ልማት ኢንቨስትመንቶችን ለማበረታታትና ለመደገፍም ህብረቱ ባስጀመረው የግሎባል ጌትዌይ ማዕቀፍ እየተሰራበት መሆኑን አስረድተዋል። የአውሮፓ ህብረት፣ ፈረንሳይ እና ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር በሀገሪቱ ያለውን የኤሌክትሪክ እና የዲጂታል መሰረተ-ልማትን ለማዘመን የሚያስችል የትብብር ማዕቀፍ ወደ ሥራ መግባቱንም ተናግረዋል። የአውሮፓ ሕብረት አባል ሀገራትና የኢትዮጵያ በርካታ ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት በትምህርትና በምርምር ዘርፍ ጭምር ትልቅ ፍሬ እያፈራ መሆኑን አስረድተዋል። የሁለቱ ወገኖች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ግንኙነትና የእርስ በእርስ ጉብኝቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱም የትብብር አድማሱን ወደላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን እንደሚያሳይ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አውሮፓ ከተሞች የሚያደርገው በረራ ትስስሩን እያሰፋ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያና አውሮፓ የረጅም ዘመን ትብብራቸውን እ.አ.አ ከ2016 ጀምሮ ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ያሳደጉ ሲሆን፥ በሁሉም መስክ የላቀ ትብብርን ለመፍጠር ህብረቱ በቁርጠኝነት ይሠራል ብለዋል።
ፓርቲዎች ለምክክሩ ስኬታማነት እያበረከቱ የሚገኘውን አስተዋፅኦ ሊያጠናክሩ ይገባል
Jul 2, 2026 1319
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018(ኢዜአ)፡- የፖለቲካ ፓርቲዎች ለምክክሩ ስኬታማነት እያበረከቱ ያለውን አስተዋፅኦ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስገነዘበ። የጋራ ምክር ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አድርጓል። በውይይቱ ላይ የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ፣ የጋራ ምክር ቤቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቀራርበው በሀገራዊ ጉዳይ ላይ በጋራ መስራት እንዲችሉ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት በተቀናጀ መልኩ የፖለቲካ ተሳትፎ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ይህ በጎ ጅምር የበለጠ እንዲጠናከር እና ለሀገረ መንግስት ግንባታው በጎ አስተዋጽኦ እንዲኖረው ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት በጋራ መቆም ይገባል ብለዋል። በመሆኑም በጋራ ምክር ቤቱ ስር የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ምክክር ስኬታማ እንዲሆን ድርሻቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የጋራ ምክር ቤቱ ጸሐፊ አቶ ታሪኩ ድምበሩ በበጀት ዓመቱ መደበኛ ውይይቶችን በአግባቡ በማካሄድ በፓርቲዎቹ መካከል ያለው ግንኙነት መጠናከሩን ገልጸዋል። ይህም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊ እና አካታች በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የራሱ አስተዋጽኦ እንደነበረው ተናግረዋል። ይህ በጎ ጅምር በቀጣይ በብሔራዊ ጥቅም እና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመቆም የሰለጠነ የፖለቲካ ባህልን ለማዳበር ያግዛል ሲሉም ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ በ2019 በጀት ዓመት አደረጃጀቱን የበለጠ በማጠናከር ሰላማዊ የፖለቲካ ባህል እንዲዳብር ሚናውን ያጠናክራል ያሉት ደግሞ የበጀት ዓመቱን የትኩረት አቅጣጫ ያቀረቡት የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሞገስ ኢደኤ ናቸው። በአዲሱ በጀት ዓመት ምክር ቤቱ እስከ ዞንና ወረዳ ድረስ ያደራጀው መዋቅር ውጤታማ በሆነ መልኩ ስራውን እንዲሰራ ይደረጋል ነው ያሉት። የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የጋራ ምክር ቤቱ በየጊዜው የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቅረፍ ረገድ ውጤታማ ስራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። በቀጣይም መደበኛ ውይይቶችን በማስቀጠል፣ ሰላማዊ እና የዘመነ የፖለቲካ ባህል እንዲኖር በመተባበር ሊሰራ እንደሚገባም አመልክተዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባላት ዛሬ ጠዋት በሸገር ከተማ ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አሳርፈዋል።
ፖለቲካ
መከላከያ ሠራዊት የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት እየጠበቀ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Jul 4, 2026 680
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝነት እየጠበቀ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተመራቂዎች አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላምና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር)፣ የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ጥላሁን ደምሴ እና ከፍተኛ ጄኔራል መኮንኖች ተገኝተዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሥነ-ስርዓቱ ባስተላለፉት፤ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ የደህንነት ሁኔታ ውስብስብና ኢ-ተገማችነትን ታሳቢ ያደረገ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ የታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች የሴራ ጥምረት ወይም "ፅምዶ" ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊ ሰላምና ደህንነት በመጠበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለዘመናት በሰላም እጦት የሚገለፀው የቀይ ባሕርና አፍሪካ ቀንድ አከባቢ የደህንነት ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ እየተወሳሰበ መምጣቱን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው የምትገኝ፣ ከማንኛውም የቀጣናው ችግርና ተጠቃሚነት ማምለጥ የማትችል ትልቅ ሀገር መሆኗንም አስገንዝበዋል። ታሪካዊ ጠላቶችም ኢትዮጵያ ቀጣናውን የማረጋጋት የመሪነት ሚና እንዳትወጣና በውስጥ ጉዳዮች ብቻ እንድትጠመድ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በሌላ በኩልም ጎረቤቶችን እንዲታመሱ በማድረግ ለውስጣዊ ደህንነታችን ጫና መፍጠር የሚችሉ ሴራዎችን በመሸረብ ቀጣናውን ለማተራመስ አበክረው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ከባሕር ዳርቻ ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ ፅምዶ በሚል ስያሜ ዕድሳት ተደርጐለት እየተስተጋባ ነው ብለዋል። የዘመኑ ጦርነት በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በረጅም ርቀት ሚሳኤሎች፣ በሰው አልባ መሣሪያዎችና በሳይበር ኦፕሬሽኖች የታገዘ የቴክኖሎጂ ጦርነት መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም አደረጃጀቱንና ዘመናዊ ትጥቁን በማጠናከር በማንኛውም አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ቁመና ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ተመራቂዎችም የቀሰሙትን ስትራቴጂክ ዕውቀት ለሠራዊቱ ተጨማሪ ግንባታ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አሳስበዋል። የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ጥላሁን ደምሴ በበኩላቸው፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት የተመሰረተው ኮሌጁ በተለዋዋጭ ስትራቴጂክ ምህዳር ውስጥ የብሔራዊ ኃይል ማስፈፀሚያ አቅሞችን ውጤታማ ለማድረግ እየሰራ ነው ብለዋል። ኮሌጁ የስርዓተ ትምህርት ማሻሻያ በማድረግ በጥናት፣ ምርምርና የደህንነት ትንተና ላይ ትኩረት አድርጎ የአመራር አቅም ግንባታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል። መንግሥት የኮሌጁን የመሰረተ ልማትና የዲጂታላይዜሽን አቅም በማሳደግ ወደ ስማርት ኮሌጅ ለመቀየር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የአስተዳደሩ ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት ተገኝቷል
Jul 3, 2026 1157
ድሬደዋ፤ ሰኔ 26/2018(ኢዜአ)፦) የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የአስፈጻሚውን አካላት ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት መገኘቱን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አፈጉባኤ አብዲ ሙክታር ገለጹ። ምክር ቤቱ የስራ ዘመኑን መደበኛ ጉባኤ የፊታችን ሰኞ ያካሂዳል። የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር፣ ምክር ቤቱ የአስፈፃሚውን አካላት የአምስት አመታት የስራ እቅድና አፈጻጸም የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን አስመልክተው ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴዎቹና በሚቀርቡ ሪፖርቶች የተቀናጀ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ውጤታማ ስራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል ብለዋል። በሌላ በኩል የፍርድ ቤቶችን የአደረጃጀት፣ የበጀት እና በዳኞች ሹመት ላይ ቁጥጥር በማድረግም ለፍትህ ስርአቱ ስኬት የበኩሉን መወጣቱን አንስተዋል። ምክር ቤቱ አስፈጻሚው አካል የህዝብን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የወጡ ህጎችና ደንቦች ከህገ መንግስቱ ጋር በተናበበ መልኩ ስራ ላይ መዋሉን ሲከታተል መቆየቱን አንስተዋል። የኢኮኖሚ ዘርፎች በተቀናጀ መንገድ እንዲተገበሩ ድጋፍ በማድረግም ለውጤቱም የድርሻውን ማበርከቱን አንስተዋል። በመጪው ሰኞ በሚካሄደው በ3ኛው የስራ ዘመን 5ኛው አመት 12ኛው መደበኛ ጉባኤውም የአስፈጻሚውንና የምክር ቤቱ ተጠሪ ተቋማትን የ2018 በጀት አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ይገመግማል ብለዋል። በተጨማሪ የ2019 በጀት አመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።
በምክር ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች የውክልና ተሳትፎ ማደግ በሃሳብ ክርክር ላይ የተመሰረተ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ወሳኝ ነው
Jul 3, 2026 1027
አሶሳ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፡- በምክር ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች የውክልና ተሳትፎ ማደግ በሃሳብ ክርክር ላይ የተመሰረተ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ላለፉት በርካታ ዓመታት በአንድ ገዥ ፓርቲ ፍጹም ቁጥጥር ስር የነበረና የተፎካካሪ ፓርቲዎች ሚና እጅግ የተገደበ የነበረበት መሆኑ ይታወቃል። በሀገሪቱ የመጣውን የፖለቲካ ለውጥ ተከትሎ በተካሄዱት ጠቅላላ ምርጫዎች ግን፣ የምርጫ ሥርዓቱን ነጻ፣ ገለልተኛና ታማኝ ለማድረግ በርካታ የህግና የተቋማት ማሻሻያዎች ተደርገዋል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም ቀደም ባሉት ምርጫዎች የነበረው የተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎና የህዝብ ውክልና ዝቅተኛ የነበረ ቢሆንም፣ በሂደት በተደረጉ የፖለቲካ ሪፎርሞችና የውይይት መድረኮች ፓርቲዎች በነጻነት የመንቀሳቀስና አማራጭ ሃሳቦቻቸውን ለህዝብ የማቅረብ ዕድላቸው እያደገ መጥቷል። ይህ ውጤት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ የህዝብ ድምፅ አግኝተው የፖለቲካ ሥልጣን መጋራትና አማራጭ ሃሳብን ማሰማት የሚችሉበት ምህዳር እየተፈጠረ መሆኑን አመላካች ነው ተብሏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም የብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በመያዝ ያሸነፈ ሲሆን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም ከበፊቱ የተሻለ የክልል ምክርቤት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ አግኝተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንደተናገሩት፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳር እያደገ መምጣቱ የታየበት ነው። የቤኒሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ቤሕነን/ ፓርቲ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የነበረው የፖለቲካ ተሳትፎ ሀሳብ ብቻ ገዢ እና አሸናፊ የሆነበት ነው ብለዋል። ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ አካታች የሆነ የፖለቲካ ትርክትን መከተል እንደሚያስፈልግ ገልፀው፥ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በሁሉም መስክ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በቀጣይ በአሸናፊው የብልጽግና ፓርቲ የሚመሠረተው መንግሥት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ታሳቢ ማድረግ እንዳለበትና ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከመንግስት ጋር አብረው ለመስራት ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባም ጠቁመዋል። ይህም የፖለቲካ ፓርቲዎችን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር እና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እንዲዳብር የሚያግዝ ነው ብለዋል። ፓርቲያቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች ማግኘቱን የተናገሩት አቶ አብዱሰላም፤ ከክልሉ መንግስት ጋር የጀመሩትን ትብብር በማጠናከር ለክልሉ ሰላምና ልማት በጋራ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጉሕዴን) ማዕከላዊ ኮሚቴ ፀሐፊ አቶ ለሜሳ ኔኖ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባገኘው መቀመጫ ከመንግሥት ጋር የበለጠ ተቀራርቦ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም የሁሉንም ህዝብ ድምጽ በመስማትና የበለጠ ሀገራዊ ሀላፊነት እንደተረከበ ከግምት ውስጥ በማስገባት በሙሉ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል።
በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችሉ ናቸው
Jul 3, 2026 990
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው አሳታፊና አካታች ዐበይት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን በስልጡን የምክክር መፍትሔ ለመስጠት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሰናድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ከሚቀጥለው ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሂደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤም ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። በአጀንዳዎቹም የሀገር ግንባታ፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደርና ሰላም ግንባታ ናቸው። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉትም፤ የሀገራዊ ምክክሩ ስምንት የዋናው ጉባኤ የምክክር ዐበይት አጀንዳዎች የኢትዮጵያን ወሳኝ ጉዳዮች የያዙ ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩም በዜጎች መካከል ለዘመናት የሚነሱ የአለመግባባት ሃሳቦችን በምክክር በመፍታት በሁሉም መስክ የጋራ የፖለቲካል ኢኮኖሚ አቅም መገንባት እንደሚያስችል ገልጸዋል። አስተያየት ሰጪዎች መካከል መቶ አለቃ ጋዲሳ አብዲ፤ የሀገራዊ ምክክሩ የህዝብ አሳታፊና አካታችነት በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን ለመገንባት ወሳኝ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። የዋናው ጉባኤ ቁልፍ አጀንዳዎችም የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት በማስቀጠል በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያስችሉ ገልጸዋል። ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ገዛኸኝ ደሜ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ የዘመናት ቅራኔን በውይይትና ስምምነት መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ስምንቱ ዐበይት አጀንዳዎችም የህዝብን ፍላጎቶችና ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ማሸጋገር እንደሚያስችሉ ተናግረዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የህዝብ ተሳትፎና አካታችነት በመሰረታዊ የልማትና ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ መግባባትን በመፍጠር የጋራ ዕድገትን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ለማ ወተሬ ናቸው። በዋናው የምክክር ጉባኤ የሚመክሩ የህዝብ ወኪሎችም ስልጡን ምክክር በማድረግ ለሀገርና ህዝብ የሚጠቅሙ መፍትሔዎችን ማፍለቅ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ወጣት ክብሬ አባረዳ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር በጋራ አስተሳሰብና ፍላጎት የምትገነባ ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ መሰረት ይጥላል ብሏል። በዐበይት አጀንዳነት የሚመከርባቸው ጉዳዮችም ከህዝብ የመነጩና ለሀገራዊ ዕድገትና ሰላም መግባባትን ለመገንባት የሚበጁ መሆናቸውን ገልጿል።
የምክክር አጀንዳዎቹ የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና ጠንካራ አንድነትን ለመፍጠር ወሳኝ ናቸው
Jul 3, 2026 954
ቦንጋ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ):-ለዋናው የምክክር ጉባኤ የተለዩ አጀንዳዎች የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና ጠንካራ ሀገራዊ አንድነትና መግባባትን ለመፍጠር ሚናቸው የላቀ መሆኑን የቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ መምህራን ገለፁ። በሀገሪቱ ዘመናትን ያስቆጠሩ አለመግባባቶች በውይይት ለመፍታት ቁልፍ መሳሪያ የሆነው ሀገራዊ ምክክር በርካታ ሂደቶችን አልፎ ወደመቋጫው ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓም በሚያካሂደው ዋናው የምክክር ጉባኤም ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ለይቶ ይፋ አድርጓል። ተደራጅተው በቀረቡ የምክክር አጀንዳዎች ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ ምሁራን በኮሚሽኑ የተለዩ አጀንዳዎች ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ዋና ዋና ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ጠንካራ ሀገራዊ አንድነትና መግባባትን ለመፍጠር ጉልህ ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኮሌጁ የስነዜጋ እና ስነምግባር ትምህርት ክፍል መምህር እንግዳ ገብረማርያም እንደገለጹት፣ ችግሮችን በውይይትና በምክክር መፍታት የስልጣኔ መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሸን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ያሰባሰባቸውና አደራጅቶ ያቀረባቸው የምክክር አጀንዳዎች ልዩነቶችን ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የሚያስችሉ ናቸው። ይህም ለዘመናት ለቅራኔ ምንጭ የነበሩና የማያግባቡ ችግሮች በመፍታት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የተለያዩ ሂደቶችን አልፎ የሁሉንም አካባቢዎችና የህብረተሰብ ክፍሎች የሚወክሉ አጀንዳዎችን ለይቶ ማቅረቡ የሚደነቅ መሆኑን ያነሱት መምህር እንግዳ፣ ብዙ ውጣውረዶችን ያለፈው ምክክር ስኬታማ እንዲሆን የሁሉም አስተዋጾ ያስፈልጋል ብለዋል። በኮሌጁ የጂኦግራፊና የአካባቢ ጥናት ትምህርት ክፍል መምህር አለማው ብሩ በበኩላቸው፣ አለመግባባቶችን በውይይት መፍታትን ባህል ማድረግ ለጠንካራ ሀገረ መንግት ግንባታ ሁነኛ መሳሪያ መሆኑን አንስተዋል። እንደሀገር ባለፉት ዘመናት የተፈጠሩ ልዩነቶችን በውይይትና በምክክር ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ብዙ ሂደቶችን አልፎ ወደመቋጫ ምዕራፍ ላይ መድረሱን አድንቀው፣ ምክክሩ የሚፈለገውን ውጤት እንዲያመጣ ታሪካዊ ዕድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባናል ብለዋል። ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የነቃ ተሳትፎ በማድረግና ይህን ወርቃማ ዕድል ወደውጤት መቀየር አስፈላጊ መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል። የሀገረ መንግስት ግንባታ፣ የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርአት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሂደት፣ የፌደራል ከተሞች (አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ የሐይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነት ለዋናው ጉባኤ ከተለዩ አጀንዳዎች መካከል ይገኙበታል። በተጨማሪም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች፣ ሙስና እና መልካም አስተዳደር፣ ሰብአዊ መብቶች፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እንዲሁም የሰላም ግንባታ ጉዳዮች ምክክር የሚደረግባቸው ነጥቦች መሆናቸውም መገለጹ ይታወሳል።
የሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የኢትዮጵያን የተስፋ ጉዞ የሚወስን ልዩ የታሪክ ምዕራፍ ነው - ምሁራን
Jul 3, 2026 1157
አዲስ አበባ ፤ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የኢትዮጵያን የተስፋ ጉዞ የሚወስን ልዩ የታሪክ ምዕራፍ ነው ሲሉ አንጋፋ ምሁራን ገለጹ፡፡ ዜጎች ለምክክሩ ስኬታማነት እስካሁን ያሳዩትን የነቃ ተሳትፎ ማጠናክር እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰኔ 17 ቀን 2018 ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ የተለያዩ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ይፋ አድርጓል፡፡ እነኚህም ዋና ዋና የጉባኤው አጀንዳዎችም የሀገር ግንባታ፤ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት፤ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ፤ የሃይማኖት ጉዳዮች፤ የተቋማት ግንባታ፤ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፤ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፤ ሙስናና መልካም አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ናቸው፡፡ በእነኚህ ዋና ዋና አጀንዳዎች ዙሪያም ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ በሚጀምረው ጉባኤ ምክክር ይካሄድባቸዋል፡፡ የሀገራዊ ምክክሩ የእስካሁኑ ጉዞ፤ እውነተኛ አሳታፊነትን፣ ፍፁም ግልጽነትን እና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በማካተት ስራዎችን በስኬት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የታሪክ ኤምሬተስ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ሀገራዊ ምክክሩ ስር የሰደዱ ችግሮች የሚፈቱበት አማራጭ የሌለው ሂደት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን ከሚያራርቃቸው ጉዳዮች ይልቅ የሚያቀራርቧቸው እንደሚበልጡ ነው የጠቆሙት፡፡ ይህም ምክክሩ ችግሮችን በሰከነ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ልዩ የታሪክ አጋጣሚ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አማካሪ ፕሮፌሰር አድማሱ ገበየሁ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክሩ በመመካከርና በመነጋገር የጋራ ግንዛቤ የሚፈጠርበት ትልቅ መድረክ ነው። ይህ ሂደት ኢትዮጵያን በተሟላ ሁኔታ ተጠቃሚ እንደሚያደርግና ምክክሮቹም ወደ ሀገራዊ መግባባት የሚወስዱ ናቸው ብለዋል፡፡ የምክክር ኮሚሽኑ እስካሁን የተጓዘበት ሂደት የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም የህዝብ ተሳትፎን ከማረጋገጥ አኳያ የተመዘገበው ስኬት በሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ታይቶ የማይታወቅ መሆኑን ገልጸዋል። የፖለቲካል ሳይንስ ተመራማሪና የህግ ጠበቃው ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል እየተቀየረ ለመምጣቱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክክሩ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት እንዳይግባቡ ያደረጓቸውን መሠረታዊ ችግሮች ራሳቸው መፍትሄ እንዲያስቀምጡላቸው በር የሚከፍት መሆኑን ጠቁመዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያዊያን ስር የሰደዱ ችግሮችን በጥልቀት መመካከር አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሄዎችን ለማምጣት ሁነኛ መንገድ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ለምክክሩ መሳካት ወጣቶችና ምሁራን እንዲሁም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በባለቤትነትና በሃላፊነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ጠቅሰዋል፡፡
የኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት ግንኙነት በሁሉም መስክ ወደ ላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው - አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር
Jul 2, 2026 1987
አዲስ አበባ፣ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት ግንኙነት በሁሉም መስክ ወደ ላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ገለጹ። አምባሳደር ሶፊ ኢመስበርገር ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት ታሪካዊ ግንኙነት ስኬታማ የትብብር ዕድገት እያስመዘገበ ነው። ለአብነትም ከወራት በፊት የኢትዮ-አውሮፓ የንግድ ፎረም በርካታ የኢትዮጵያና የአውሮፓ ኩባንያዎች በተሳተፉበት በፈረንሳይ ፓሪስና በአዲስ አበባ መካሄዱን አስረድተዋል። ፎረሙ የኢትዮ-አውሮፓን የኢኮኖሚ ግንኙነት ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን ወደ አውሮፓ ለመጓዝ የቪዛ ማመልከቻቸውን ከ45 ቀናት በፊት ማስገባት እንዳለባቸው የሚደነግገው የቪዛ ገደብ መነሳቱም የንግድና የባህል ግንኙነትን እያጠናከረ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት፣ ዲጂታላይዜሽን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪና የጤና ጥበቃ ስኬቶችም ከአውሮፓ ሕብረት የልማት መርሃ ግብር ጋር በእጅጉ የሚጣጣም መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም በኢትዮጵያ የሚደረጉ የመሰረተ ልማት ኢንቨስትመንቶችን ለማበረታታትና ለመደገፍም ህብረቱ ባስጀመረው የግሎባል ጌትዌይ ማዕቀፍ እየተሰራበት መሆኑን አስረድተዋል። የአውሮፓ ህብረት፣ ፈረንሳይ እና ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር በሀገሪቱ ያለውን የኤሌክትሪክ እና የዲጂታል መሰረተ-ልማትን ለማዘመን የሚያስችል የትብብር ማዕቀፍ ወደ ሥራ መግባቱንም ተናግረዋል። የአውሮፓ ሕብረት አባል ሀገራትና የኢትዮጵያ በርካታ ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት በትምህርትና በምርምር ዘርፍ ጭምር ትልቅ ፍሬ እያፈራ መሆኑን አስረድተዋል። የሁለቱ ወገኖች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ግንኙነትና የእርስ በእርስ ጉብኝቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱም የትብብር አድማሱን ወደላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን እንደሚያሳይ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አውሮፓ ከተሞች የሚያደርገው በረራ ትስስሩን እያሰፋ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያና አውሮፓ የረጅም ዘመን ትብብራቸውን እ.አ.አ ከ2016 ጀምሮ ወደ ስትራቴጂክ አጋርነት ያሳደጉ ሲሆን፥ በሁሉም መስክ የላቀ ትብብርን ለመፍጠር ህብረቱ በቁርጠኝነት ይሠራል ብለዋል።
ፓርቲዎች ለምክክሩ ስኬታማነት እያበረከቱ የሚገኘውን አስተዋፅኦ ሊያጠናክሩ ይገባል
Jul 2, 2026 1319
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018(ኢዜአ)፡- የፖለቲካ ፓርቲዎች ለምክክሩ ስኬታማነት እያበረከቱ ያለውን አስተዋፅኦ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስገነዘበ። የጋራ ምክር ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አድርጓል። በውይይቱ ላይ የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ፣ የጋራ ምክር ቤቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቀራርበው በሀገራዊ ጉዳይ ላይ በጋራ መስራት እንዲችሉ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት በተቀናጀ መልኩ የፖለቲካ ተሳትፎ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ይህ በጎ ጅምር የበለጠ እንዲጠናከር እና ለሀገረ መንግስት ግንባታው በጎ አስተዋጽኦ እንዲኖረው ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት በጋራ መቆም ይገባል ብለዋል። በመሆኑም በጋራ ምክር ቤቱ ስር የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ምክክር ስኬታማ እንዲሆን ድርሻቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የጋራ ምክር ቤቱ ጸሐፊ አቶ ታሪኩ ድምበሩ በበጀት ዓመቱ መደበኛ ውይይቶችን በአግባቡ በማካሄድ በፓርቲዎቹ መካከል ያለው ግንኙነት መጠናከሩን ገልጸዋል። ይህም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊ እና አካታች በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የራሱ አስተዋጽኦ እንደነበረው ተናግረዋል። ይህ በጎ ጅምር በቀጣይ በብሔራዊ ጥቅም እና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመቆም የሰለጠነ የፖለቲካ ባህልን ለማዳበር ያግዛል ሲሉም ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ በ2019 በጀት ዓመት አደረጃጀቱን የበለጠ በማጠናከር ሰላማዊ የፖለቲካ ባህል እንዲዳብር ሚናውን ያጠናክራል ያሉት ደግሞ የበጀት ዓመቱን የትኩረት አቅጣጫ ያቀረቡት የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሞገስ ኢደኤ ናቸው። በአዲሱ በጀት ዓመት ምክር ቤቱ እስከ ዞንና ወረዳ ድረስ ያደራጀው መዋቅር ውጤታማ በሆነ መልኩ ስራውን እንዲሰራ ይደረጋል ነው ያሉት። የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የጋራ ምክር ቤቱ በየጊዜው የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመቅረፍ ረገድ ውጤታማ ስራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። በቀጣይም መደበኛ ውይይቶችን በማስቀጠል፣ ሰላማዊ እና የዘመነ የፖለቲካ ባህል እንዲኖር በመተባበር ሊሰራ እንደሚገባም አመልክተዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባላት ዛሬ ጠዋት በሸገር ከተማ ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አሳርፈዋል።
ማህበራዊ
በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች ከአካባቢው ጸጋ እና ከኢንዱስትሪ ፍላጎት ጋር መጣጣም ይጠበቅባቸዋል
Jul 4, 2026 165
ወልቂጤ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚሰጧቸው ስልጠናዎች ከአካባቢ ፀጋ እና ከኢንዱስትሪው ፍላጎት ጋር መጣጣም እንዳለባቸው የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ የስልጠና መስክ ልየታ ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና በወልቂጤ ከተማ ሰጥቷል፡፡ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር ሰለሞን ፈርሻ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አዲሱ የስልጠና ልየታ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ገበያው እና ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን የሰው ኃይል ማፍራት ላይ እንዲያተኩሩ የሚያስችል ነው። በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ ተመስርተው የልህቀት ማዕከል በመሆን ዘመኑን የዋጀ እውቀትን ማስረጽ ላይ አተኩረው መስራት እንዳለባቸውም ተናግረዋል። የአካባቢውን የልማት እንቅስቃሴ እና ጸጋ መጠቀም የሚችል የሰለጠነ ብቁ የሰው ሃይል በማፍራት የሰልጣኞችን ተመራጭነትና ተወዳዳሪነት ማሳደግ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የክልሉ ፖሊሲ ጥናት እና ምርምር ኢንስቲትዩት ተመራማሪ አበራ ኤልያስ (ዶ/ር) ፤ ኮሌጆች በአካባቢያዊ ፀጋ እና በሥራ ገበያ ፍላጎት መሰረት ወቅቱን የዋጀ ሙያ ላይ አተኩረው እንዲሰሩ ጥናት ተደርጓል ብለዋል። ይህም ሰልጣኞች የተሻለ ክህሎትና እውቀት ይዘው ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፣ ይህም ተቋማቱ ተወዳዳሪ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት ያስችላቸዋል ብለዋል። የወራቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አካዳሚክ ዘርፍ ምክትል ዲን ወይዘሮ ሶፍያ ዋበላ በበኩላቸው፤ አዲሱ የትምህርት ስልጠናና ስትራቴጂ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ ለትምህርትና ስልጠና ጥራት መረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። ስትራቴጂው በኢንዱስትሪ እና በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችና ወቅታዊ ሁኔታዎችን ባገናዘበ መንገድ በገበያው ተወዳዳሪ የሚሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል መሆኑንም አስረድተዋል። በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስኮች ልየታ አምራች፣ ግብርና፣ ቱሪዝም እና አገልግሎት ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ የስልጠና መስኮች የአካባቢ እና የሃገር እድገት ፍላጎትን መሰረት ያደረገ መሆኑ ለዘርፉ ውጤታማነት ወሳኝ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መምሪያ ሃላፊ አቶ አህመዲን ጀማል ተናግረዋል። የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የኢንዱስትሪውን ፍላጎት የሚያሟላ ብቃት ያለው የሰው ሀይል በተግባር እና በንድፈ-ሃሳብ ትምህርት ታግዘው እንዲያሰለጥኑ የሚያስችላቸው መሆኑንም ተናግረዋል። በመድረኩ የክልሉ የዘርፉ አመራሮችን ጨምሮ የዞንና የልዩ ወረዳ የቴክኒክና ሙያ መምሪያ ሃላፊዎች፣ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲኖች እና የዘርፉ አጥኚዎች ተሳትፈዋል።
በክልሎች የመምህራንን አቅም በመገንባትና የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ብቁ ዜጋ የማፍራት ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jul 4, 2026 123
ሆሳዕና/ዲላ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች የመምህራንን አቅም በመገንባትና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ተደራሽ በማድረግ ብቁ ዜጋ የማፍራት ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሎቹ ትምህርት ቢሮዎች ገለጹ። የሆሳዕና እና የዲላ ትምህርት ኮሌጆች በተለያዩ የትምህርት መሰኮች ያሰለጠኗቸውን 2ሺህ 20 እጩ መምህራንን በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዲፕሎማ እና በሰርተፍኬት ዛሬ አስመርቀዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፣ በክልሉ ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ተደራሽ በማድረግ በእውቀት የበቁ ዜጎችን ለማፍራት እየተሰራ ነው። የትምህርት ኮሌጁ ከቅድመ አንደኛ እስከ መካከለኛ ደረጃ የሚያስተምሩ መምህራንን በብቃት በማሰልጠን ኮሌጁ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ክልሉ የበኩሉን ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል። ምሩቃን በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን እውቀት በመጠቀም በቀጣይ በስነ ምግባር የታነፁና ሀገራቸውን የሚያሳድጉ ዜጎችን ማፍራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። በክልሉ የመምህራንን አቅም በመገንባትና የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ብቁ ዜጋ የማፍራት ሥራው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የኮሌጁ ዲን አባይነህ ኤርጎጎ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኮሌጁ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ መሰረት ብቁ መምህራን እያፈራ መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬም ኮሌጁ ለ20ኛ ዙር በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዲፕሎማና በሰርተፍኬት ያሰለጠናቸውን 1ሺህ 51 መምህራንን አስመርቋል ብለዋል። በዲግሪ መርሀግብር ከእንግሊዝኛ ትምህርት ክፍል 3 ነጥብ 98 በማምጣት በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀችው ኤልሳቤት ፈለቀ፤ በኮሌጅ ቆይታዋ በቀጣይ ብቁ ተማሪዎችን ለማፍራት የሚያስችል እውቀት ማግኘቷን ተናግራለች። መምህርነት ትውልድን በላቀ ትጋት፣ በታማኝነትና በቅንነት በመቅረፅ ረገድ ትልቅ ሀላፊነት ያለበት ሙያ መሆኑን ተናግራለች። በኮሌጁ ባገኘው አውቀት በታማኝነትና በቅንነት ለማገልገል መዘጋጀቱን የተናገረው ደግሞ በዲፕሎማ መርሃ ግብር ከሒሳብ ትምህርት ክፍል በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀው ደግነት ስምኦን ነው። በተመሳሳይ የዲላ ትምህርት ኮሌጅ ለ13ኛ ዙር በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዲፕሎማና በሰርተፍኬት ያሰለጠናቸውን 969 እጩ መምህራንን ዛሬ አስመርቋል። በምረቃው ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንዳሉት፤ በክልሉ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻልና የመምህራንን አቅም በማሳደግ የመማር ማስተማር ሥራውን ውጤታማ ለማድረግ ሲሰራ ቆይቷል። የዲላ ትምህርት ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በዲግሪ ደረጃ መምህራን ማፍራቱ ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑንም ጠቅሰዋል። መምህርነት ትውልድ የሚቀረጽበትና ሀገር የሚገነባበት ታላቅ ጥበብ ነው ያሉት ሃላፊው፣ እጩ ምሩቃን ያለባቸውን ከፍተኛ ሃላፊነት ተገንዝበው ለትምህርት ጥራት መጠናከር የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። ኮሌጁ ለመጀመሪያ ጊዜ በዲግሪ መርሃ ግብር ማስመረቁ እለቱን ለየት ያደርገዋል ያሉት ደግሞ የኮሌጅ ዲን ተረፈ ሾጣ ናቸው። በዛሬው እለት በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዲፕሎማና በሰርተፍኬት ያሰለጠናቸውን 969 እጩ መምህራ መመረቃቸውን ገልጸዋል፣ ምሩቃን በቀጣይ ለሀገር እድገት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር በሃላፊነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። በኮሌጁ ከጄኔራል ሳይንስ ትምህርት ክፍል በመጀመሪያ ዲግሪ የዋንጫ ተሸላሚ የሆነችው የምስራች ምትኩ በበኩሏ፤ መንግስት ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት የሰጠው ልዩ ትኩረት ዘርፉን ለመቀላቀል እንዳነሳሳት ገልጻለች። በቀጣይ በመምህርነት ሙያዋ ሕጻናትን በጥሩ ስነምግባር ኮትኩቶ ለማሳደግ ዝግጁ መሆኗን ተናግራለች።
ጤናማና አምራች ማህበረሰብ ለመፍጠር በሚከናወነው የተቀናጀ ጥረት ውጤት እየተገኘ ነው
Jul 4, 2026 126
ድሬዳዋ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገሪቱ ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ ጤናማና አምራች ማህበረሰብ ለመፍጠር በሚከናወነው የተቀናጀ ጥረት ውጤት እየተገኘ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ አስታወቁ። በድሬደዋ አስተዳደር በ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የቢፍቱ አጠቃላይ ሆስፒታል ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ሆስፒታሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃርና የድሬዳዋ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፅጌረዳ ክፍሌ በተገኙበት ተመርቆ ስራ ጀምሯል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ እንደ አገር ጤናማ እና አምራች ህብረተሰብ ለመፍጠር የተከናወኑ የተቀናጁ ስራዎች ውጤታማ ናቸው። በተለይም ባለፉት አምስት አመታት ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር በመንግሥት እና በግል ባለሃብቶች የተከናውኑ ስራዎች አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። መንግስት ለረዠም አመት በስራ ላይ የቆየውን የጤና ፖሊሲ በማሻሻል ወቅቱን የጠበቀና ዘመኑን የዋጃ የጤና ፖሊሲ ተግባራዊ ማድረጉን ተናግረዋል። አሁን ላይ ስራ ላይ በዋለው የጤና ፖሊሲ በሽታን ከመከላከል ባሻገር አክሞ የማዳን ስራ ትኩረት ተሰጥቶት መሠረታዊ ውጤት እንዲመዘገብ መደላድል መፍጠሩን አመልክተዋል። በድሬዳዋ አስተዳደር በግል ባለሃብት ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ጠቅላላ ሆስፒታል የዚሁ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር በበኩላቸው፤ ባለፉት የለውጥ አመታት በአስተዳደሩ በከተማና በገጠር አካባቢዎች ጤናማና አምራች ማህበረሰብ ለመፍጠር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። አስተዳደሩ የጤና ፍትሃዊ ተደራሽነትና ጥራት እንዲረጋገጥ ባከናወናቸው ተግባራት ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው በዘርፉ ባለሀብቶች ሚናቸውን እንዲወጡም ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። በዛሬው ዕለት አገልግሎት መስጠት የጀመረው ጠቅላላ ሆስፒታል የዚሁ ውጤት መገለጫ መሆኑን ጠቁመዋል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፅጌረዳ ክፍሌ በበኩላቸው፤ የሆስፒታሉ ስራ መጀመር በጤናው አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ላይ የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል ። ጠቅላላ ሆስፒታሉ ዘመናዊ መሳሪያዎችና ክፍሎችን ያካተተና ዲጂታል የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሆስፒታሉ ባለቤት ዶክተር ሱሌይማን ኢብሳ ናቸው። ሆስፒታሉ ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁመው ተገንብቶ ስራ እንዲጀምር በመንግስት በኩል ለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነዋል።
በክልሉ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራት ይጠናከራሉ
Jul 4, 2026 158
ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ ዛሬ በኮምቦልቻ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም ሴቶች በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው ኢኮኖሚያቸውን እንዲያሳድጉ፣ ሀብት እንዲያፈሩ፣ ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊትና ከጥቃት እንዲጠበቁ ለመታደግ በተሰሩ ሥራዎች አበረታች ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪ የፖለቲካ ተሳትፏቸውን በማሳደግ በውሳኔ ሰጪነትም አዎንታዊ ሚና እንዲኖራቸው መደረጉን ጠቅሰው፣ ውጤታማ ተግባራት በማከናወን ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል ብለዋል። በጤና ተቋማት የእናቶች ማቆያ እና የሴቶች ማገገሚያ ማዕከል እየተቋቋመ እንደሚገኝ የተናገሩት የቢሮ ኃላፊዋ፣ ለዚህም የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ እመቤት ደሳለኝ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በዞኑ የሴቶችን ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ለማሳደግ በተደረገ ጥረት ውጤት ተመዝግቧል። በተለይ የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸውን ሴቶች በመደገፍና የገንዘብ ብድር በመስጠት ወደሥራ ገብተው ገቢ እንዲያገኙና የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ እየተደረገ ነው ብለዋል። ሴቶችን በልማት ቡድን ጭምር በማደራጀት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል ያሉት ደግሞ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ዘቢባ አህመድ ናቸው። መንግስት፣ የተለያዩ ተቋማት እና አጋር አካላት ለሴቶች ትኩረት ሰጥተው በመስራታቸው የሚደርስባቸውን ጥቃት መከላከልና በተለያየ መንገድ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ተናግረዋል። በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢኮኖሚ
ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው
Jul 4, 2026 141
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለፁ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፣ የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት፤ የሲዳማ ክልል የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ባለሀብቶች ወደ ሀዋሳ በመምጣት እውቀትና ሀብታቸውን ተጠቅመው በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል። ሀዋሳ መተላለፊያና ማረፊያ ከተማ በመሆኗ ባለሃብቶች በአካባቢው ያለውን ዕድል እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል። ሀዋሳን በጋራ ለመገንባት የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው በቁርጠኝነት ለሰሩና የበኩላቸውን ሚና ለተወጡም ምስጋና አቅርበዋል። ሀዋሳ የደቡብ ፈርጥ፣ የሰላም ደሴት፣ ባላት ውብ ተፈጥሮ ምድረ ገነት የተባለች፣ እንዲሁም የህዝቡ እንግዳ ተቀባይነት የፍቅር ቤት ያስባላት ከተማ መሆኗን አንስተዋል። ሀዋሳን ለኑሮ፣ ለመዝናኛ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት የተመቸች ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው፣ የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ የፕሮጀክት መገንቢያ ብቻ ሳይሆን፣ የነገንና አዲሱን ምዕራፍ በጋራ ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ሀዋሳ በተፈጥሮ የታደለች ናት ያሉት ከንቲባው፤ ከተማዋን አልምቶ ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የሀዋሳ ሐይቅ የቱሪዝም ምንጭና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን አንስተው፤ የሐይቁን ዳርቻ ማልማት የከተማዋን ገጽታና ተስፋ የሚቀይር ታሪካዊ ስራ መሆኑንም ገልጸዋል። ሀዋሳን ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለቱሪዝም ምቹ እንዲሁም ከተማዋን የአፍሪካ የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የፍቅር ሐይቅ፣ አሞራ ገደልና ዓሳ ገበያን ለነዋሪዎቿና ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ መታቀዱንም ተናግረዋል። ከተማዋን በዘመናዊ መንገድ ለመገንባት ለተወጠነው ፕሮጀክት ከሦስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ በጀት እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ከዚህ መካከል ሁለት ቢሊዮን ብር ከከተማ አስተዳደሩ፣ አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብሩን በገቢ ማሰባሰቢያ ለማግኘት መታቀዱን አስረድተዋል። ባለፉት ሁለት ወራት በቀረበው ጥሪ መሰረት በመጀመሪያው ዙር የሀብት ማሰባሰቢያ ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው፤ የዛሬው መድረክም የመጀመሪያ ዙር የሀብት ማሰባሰቢያ ማጠናቀቂያ መሆኑን ተናግረዋል። የሀዋሳ ሐይቅን ለማልማት የከተማዋ ነዋሪዎች፣ ባለሃብቶችና ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የድህነትና ኋላቀርነት ታሪክን በሚሰብር የመነሳትና የብልፅግና የእጥፋት ዘመን ላይ ናት
Jul 4, 2026 129
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የድህነትና ኋላቀርነት ታሪክን በሚሰብር የመነሳትና የብልፅግና የእጥፋት ዘመን ላይ ናት ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ ሀገራት ከችግርና ጉስቁልና የሚሻገሩበት የእጥፋት ጊዜ አለ። ኢትዮጵያ ያለችበት ዘመን የእጥፋት፣ ብልፅግናና የመነሳት ዘመን መሆኑንም ተናግረዋል። በአዲስ አበባ በመንግስት መሪነት፣ በግል ባለሀብቱ ተሳትፎና ትብብር የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የሀዋሳ የልማት ፕሮጀክት ትልቅ በጀት የሚጠይቅ፤ ሲጠናቀቅም ለነገ ተጠቃሚነት ማረጋገጫ መሆኑንም ጠቁመዋል። በሁሉም አካባቢዎች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። አንድነታችንን እንደጋሻና ጦር በመጠቀም ኢትዮጵያን ከድህነትና ኋላቀርነት የምናላቅቅበትና በጋራ የምናለማበት መጪው ጊዜ ብሩህ ነው ብለዋል። መድረኩ ብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ይሁንታ አግኝቶ በተመረጠበትና ለመንግስት ምስረታ እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት መዘጋጀቱ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው ነው ብለዋል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን በመኸር እርሻ ከ485 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም ይለማል
Jul 4, 2026 177
ደብረ ማርቆስ ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ጎጃም ዞን በመጭው የመኸር ምርት ዘመን ከ485 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እርሻ እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ እንቢአለ አለኽኝ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ከ669 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥ ከ485 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በኩታ ገጠም እንደሚለማ ነው የተናገሩት። በመኸር እርሻ የምርት ማሳደጊያ ግብአት ፣ ቴክኖሎጂና አዳዲስ አሰራሮችን በተሻለ መንገድ ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም አርሶ አደሩ ከራሱ አልፎ ለገበያ የሚያቀርበው ትርፍ ምርት ለማምረት እንደሚችልም ነው የተናገሩት። ከ100 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የስንዴ፣ ጤፍ ፣ ማሽላ ፣ የቢራ ገብስ ፣ በቆሎና ቦለቄ ሰብሎችን በኩታ ገጠም ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን በተደረገው ጥረትም ክረምቱ ቀድሞ በገባባቸው አካባቢዎች ከ90 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን ተናግረዋል። በኩታ ገጠም ልማቱ ከ20 በላይ ትራክተሮች በእርሻ ስራው ላይ መሰማራታቸውን ጠቁመው ይሕም የአርሶ አደሩን ጊዜ፣ ገንዘብና ጉልበት በመቆጠብ በሌሎች የልማት ስራዎች እንዲሰማራ የሚያደርግ ነው ብለዋል። እስካሁን በኩታ ገጠም በዘር ለተሸፈነው መሬትም ከ250 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን ይህም ምርታማነትን በማሳደግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያግዝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዞኑ የደብረኤሊያስ ወረዳ የገነቴ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አየነው በቀለ እንደገለጹት፤አንድ ሄክታር መሬታቸውን በኩታ ገጠም በማልማት በቆሎ መዝራታቸውን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመትም በኩታ ገጠም ካለሙት ስንዴና በቆሎ ያገኙትን ተጨማሪ ምርት ለገበያ በማቅረብ የኢኮኖሚ አቅማቸውን ማሳደጋቸውን አስረድተዋል። የደጀን ወረዳ የኩራር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ያደለው በዛ በበኩላቸው፤ ባለፈው የምርት ዘመን ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በኩታ ገጠም ማሽላ በመዝራት ተጨማሪ የአራት ኩንታል ምርት እንዳገኙ ነው የሚገልጹት። በዘንድሮ ዓመትም ተጠቃሚነታቸውን ለማስፋት በአካባቢው ካሉ አርሶ አደሮች ጋር በጋራ በመሆን በኩታ ገጠም ማሽላን መዝራታቸውን አብራርተዋል። የኩታ ገጠም አሰራር ዘርንና ግብአት አጠቃቀምን በተመሳሳይ ጊዜ ከማካሄድ ባሻገር የሚዛመት የሰብል በሽታን፣ አረምንና ተባይን በጋራ ለመከላከል የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል። በዞኑ በመኸር ምርት በአጠቃላይ ከሚለማው ከ669 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ከ26 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት መታቀዱንም ነው ያመለከቱት።
በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jul 4, 2026 120
ቦንጋ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመሬት አያያዝና አጠቃቀምን በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ዘርፍ የአየር ንብረት አፈፃፀም የመሬት አያያዝ ፕሮግራም (CALM) የመጀመሪያ ምዕራፍ መዝጊያ መርሃ ግብር አካሂዷል። የክልሉ የግብርና ቢሮ ኃላፊ አማካሪና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ መላኩ፣ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም ያሉ የውሃ፣ መሬትና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶችን መንከባከብ ማልማትና በተገቢዉ ጥቅም ለይ ማዋል ወሳኝ በመሆኑ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተቀርፀው በመተግበር ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በሆነው (CALM) በክልሉ በ40 ወረዳዎች በውሃና መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ላይ በሰራው ስራ ምርት የማይሰጡ አሲዳማ መሬቶች እንዲያገግሙና ምርታማ እንዲሆኑ ትልቅ ሚና መጫወቱን ገልፀዋል። በተጨማሪም በፕሮግራሙ እገዛ አርሶ አደሩ መሬቱን አስይዞ የብድርና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲያገኝ የ2ኛ ዙር መሬት ልኬት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡ ክልሉ የበርካታ የተፈጥሮ ሀብቶች መገኛ በመሆኑ ይህን ሀብት በመንከባከብና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል። በፕሮግራሙ በ199 ተፋሰሶች ከ112 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት ማልማት 53 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ውብሸት ዘነበ ናቸው ። እንደ ክልል የመሬት ልኬት ከተካሄደባቸዉ 380 ሺህ ይዞታዎች ውስጥ 200 ሺህ ያህሉ በዚህ ፕሮግራም የተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በቢሮው የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ተረፈ ማሞ በበኩላቸዉ፣ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በ40 ወረዳዎች በሁለት መቶ ተፋሰሶች ላይ ማህበራትን በማደራጀት ሲሰራ ቆይቷል ነው ያሉት። በዚህም አርሶ አደሩ የተለያዩ ፍራፍሬዎችንና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ሰብሎችን በማምረት ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኝ ነው የገለጹት። በመጀመሪያዉ ምዕራፍ ለተፋሰሱ አርሶ አደሮች ለኑሮ ማሻሻያና ለተለያዩ መሰረተ ልማት ግንባታዎች ከ247 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ተናግረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት፤ ይበልጥ ተደራሽና ቀልጣፋ በመሆን የደንበኞችን እርካታ ያረጋግጣል
Jul 3, 2026 495
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት፤ የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ተደራሽና ቀልጣፋ በማድረግ የደንበኞችን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ የሚያረጋግጥ መሆኑን የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎችና ባለሙያዎች ገለጹ። አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ተደራሽ እና ጥራት ያለው ለማድረግ የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ ለማኅበረሰቡ ይበልጥ ተደራሽ በመሆን ወደ አገልግሎት የገቡት ሁለት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ ባሶች ቴክኖሎጂዎቻቸው ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት የሰጡ ናቸው፡፡ በዚህም አንደኛው ባስ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ (EV) የሚሠራ ሲሆን ሁለተኛው የተፈጥሮ ጋዝን በመጠቀም የሚንቀሳቀስና አገልግሎት የሚሰጥ ነው፡፡ እነዚህ ተንቀሳቃሽ መስኮቶች የስድስት ቁልፍ የፌዴራል ተቋማትን አገልግሎቶች የሚሰጡ ሲሆን፣ አገልግሎቶቹም ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ በመሄድ የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው፡፡ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተጠቃሚዎች እንደገለጹት፤ ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት እጅግ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገኟቸው ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ አቶ በኃይሉ ወርቁ በሰጡት አስተያየትም ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት ማኅበረሰቡ ባለበት ቦታ ሆኖ ፈጣንና የተቀላጠፈ የመንግሥት አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉን ገልጸዋል። ይህ የዲጂታል ትግበራ አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ ከሙስና የጸዳ፣ ግልጽና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑንም አክለዋል። አቶ አስቻለው ጓዴ በበኩላቸው ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት በየአካባቢው እየተዘዋወረ አገልግሎት መስጠቱ ማኅበረሰቡን ከተጨማሪ ወጪና ከተንዛዛ እንግልት እንደታደጋቸው ገልጸዋል። አሠራሩ ጊዜና ገንዘብን በአግባቡ ለመቆጠብ ያስቻለ በመሆኑም የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል፡፡ በወረፋና በተለያዩ ቦታዎች መጉላላት ሳይኖር፣ በአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን ማግኘት መቻሉ ጊዜንና ጉልበትን በከፍተኛ ደረጃ እየቆጠበላቸው መሆኑን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ወርቅነሽ እሸቱ ናቸው፡፡ የአገልግሎቱ ዲጂታላይዝ መሆን ከተገልጋዩ ባሻገር ለባለሙያዎችም የላቀ የሥራ ተነሳሽነትና ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠሩን አገልግሎቱን የሚሰጡ ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡ የአገልግሎቱ ባለሙያ አቶ አሰግድ ንዋይ እንደገለጹት፣ አዲሱ አሠራር ተቋማትና ባለሙያዎች ወደ ተገልጋዩ ይበልጥ እንዲቀራረቡና ግልጽነት የሰፈነበት አገልግሎት እንዲሰጡ አስችሏል። እሌኒ ውድነህ በበኩሏ፤ አዲሱ የዲጂታል አሠራር ለሠራተኞች ጤናማ የሥራ ድባብ ከመፍጠሩም በላይ፣ የተገልጋዮች እርካታ ለባለሙያው ትልቅ መነሳሳት መሆኑን ጠቁማ፣ ተንቀሳቃሽ መሶብ ማኅበረሰቡን በእጅጉ ማስደሰቱን ገልጻለች። የፌደራል መሶብ አገልግሎት ማዕከል ምክትል ኦፕሬሽናል ዘርፍ ኃላፊ ቤዛዊት ብርሃኔ በበኩላቸው፤ ይህ ዘመናዊ አሠራር ኅብረተሰቡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሁልጊዜም በታላቅ እምነት፣ ምቾትና አስተማማኝ በሆነ መልኩ እንዲያገኝ በር የከፈተ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል
Jul 1, 2026 1387
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻሉን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ አገልግሎቱ በተጀመረ አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ3ሺህ 600 በላይ ነዋሪዎች የዲጂታል አገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከትውልድ እስከ ሞት ያሉ ወሳኝ ኩነቶችን የሚመዘግብ ተቋም ነው፡፡ ይህንን የአገልግሎት አሰጣጡን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ሰፊ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፣ በቅርቡም አዲሱን ዲጂታል ስርዓት በስኬት አስመርቆ ስራ አስጀምሯል። ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር ነዋሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ወይም በኮምፒውተራቸው አማካኝነት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ምቹ አሰራር የፈጠረ ነው። በኦንላይን የተጀመሩት አራቱ ዋና ዋና አገልግሎቶችም መታወቂያን ከፋይዳ መረጃ ጋር ማስተሳሰር፣ የነዋሪነት መታወቂያ እድሳትና የጠፋን መተካት፣ ያላገባ የምስክር ወረቀት አገልግሎት እና የልደት ምስክርነት ወረቀት አገልግሎት ናቸው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ፤አዲሱ የዲጂታል አሰራር ጊዜን በመቆጠብ፣ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ትልቅ ጠቀሜታ እያገኙበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። ከተጠቃሚዎች መካከል የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ነዋሪ አቶ አባትዬ ተስፋዬ ፤ አገልግሎቱን በቀላሉ ከቤታቸው ሆነው በቴክኖሎጂው አማካኝነት ማጠናቀቃቸውን ገልጸው፣ የተዘጋጀላቸውን መታወቂያ ለመረከብ ብቻ ወደ ወረዳው መምጣታቸውን ተናግረዋል። ይህ አሰራር ጊዜን ከመቆጠቡ ባለፈ፣ ዘመናዊና ስልጡን አሰራር በመሆኑ ከፍተኛ እርካታ እንደፈጠረላቸውም ጨምረው አስታውቀዋል። ሌላኛው የዚሁ ወረዳ ነዋሪና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ኢሳያስ ግርማ በበኩላቸው፤ የዲጂታል አሰራሩ ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ በዘርፉ ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ አንጻር አይነተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ ሆነው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ወይም በኮምፒውተራቸው አስፈላጊውን ሰነድ አያይዘው ካመለከቱ በኋላ የሚፈልጉት አገልግሎት በፍጥነት እየተሰጣቸው ይገኛል ያሉት ደግሞ በኤጀንሲው የኦንላይን አገልግሎት ባለሙያ የሆኑት ደሳለኝ ዘርጋ ናቸው። ተገልጋዩ ወደ ወረዳ በአካል የሚመጣው የተዘጋጀውን ሰርተፊኬት ወይም መታወቂያ ለመውሰድ ብቻ መሆኑን ባለሙያው አብራርተዋል። ሌላኛዋ የኤጀንሲው የኦንላይን አገልግሎት ባለሙያ ሶስና አወል በበኩላቸው ፤ይህ አሰራር ቀደም ሲል በወረዳዎች ላይ ይፈጠር የነበረውን ከፍተኛ የህዝብ ግርግርና የአገልግሎት አሰጣጥ ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰው ይገኛል ብለዋል። ይህም ሰራተኞች በተረጋጋ መንፈስና በነጻነት ስራቸውን በጥራት እንዲያከናውኑ ትልቅ እገዛ ማድረጉን አክለዋል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሤ በበኩላቸው፤ አዲሱ የኦንላይን አገልግሎት አሰጣጥ በተቋሙ ይስተዋሉ የነበሩ የአገልግሎት መቆራረጦችንና የተገልጋይ እንግልትን በከፍተኛ ደረጃ እየቀረፈ መሆኑን አስታውቀዋል። አገልግሎቱ በተጀመረ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ3ሺህ 600 በላይ ነዋሪዎች ከቤታቸው ሆነው በቴክኖሎጂው መጠቀም መቻላቸውን ለአብነት አንስተዋል። የኦንላይን አገልግሎቱ በተገልጋይና በአገልግሎት ሰጪዎች መካከል ያለውን ቀጥተኛ ንክኪ በማስቀረት ብልሹ አሰራርን በጽኑ የሚከላከል መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂንና ስማርት ከተማ የመፍጠር ግብን የሚያሳካ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
የአገልግሎት እመርታ በመሶብ - የዜጎች እፎይታ እና የተሳለጠ አገልግሎት
Jul 1, 2026 1051
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2018 (ኢዜአ)፡-የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት በመቀነስ ፈጣን፣ ጥራት ያለውና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ወደ ሥራ የገባው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የዜጎችን እንግልት በመቀነስና የመንግሥት አሰራርን በማዘመን ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ነው። ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አሰራርን በአንድ ቦታ ላይ በማቅረብ፣ ዜጎች የሚፈልጓቸውን አገልግሎቶች ያለምንም ውጣ ውረድ ፈጣን፣ ጥራት ያለውና ምቹ በሆነ ሁኔታ እንዲያገኙ አድርጓል። ይህም የመንግሥትን አገልግሎት አሰጣጥ ከማሳለጡ ባለፈ፣ አጠቃላይ አሰራሩን ግልጽ በማድረግ ብልሹ አሰራርን በከፍተኛ ሁኔታ መከላከል ችሏል፡፡ የማዕከሉን አገልግሎት በተመለከተ ለኢዜአ አስተያየት የሰጡት የመዲናዋ ነዋሪ አቶ ደስታ ወዳጄነህ፣ የዲጂታል መሶብ አገልግሎት መዘርጋቱ ውድ ጊዜን የሚቆጥብና ኢትዮጵያ ወደ ላቀ የአገልግሎት ምዕራፍ እየገባች መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል። አሰራሩ ዜጎች በቀላሉ አገልግሎት እንዲያገኙ በማስቻል ጊዜያቸውን በአግባቡ ለመጠቀም እንደረዳቸውና ቀደም ሲል ትልቅ ፈተና የነበረውን እንግልት ያስቀረ አሠራር መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሌላኛው ነዋሪ አቶ ዮሴፍ ታመነ በበኩላቸው፣ ቀደም ሲል መታወቂያ ለማውጣት ብዙ መመላለስና አድካሚ ውጣ ውረዶች የነበሩ መሆኑን አስታውሰው፣ አሁን ግን በአዲሱ አሰራር ፈጣን አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ረጅም ጊዜ ይወስድ የነበረው አገልግሎት በአሁኑ ወቅት በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ እንዲጠናቀቅ መደረጉ ነዋሪዎች በእለት ተእለት እንቅስቃሴያቸው ጊዜያቸውን እንዲቆጥቡና በቅልጥፍና እንዲስተናገዱ እንዳገዛቸው ጠቁመዋል፡፡ ይህም በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ውስጥ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችንና ተያያዥ ቅሬታዎችን ሙሉ በሙሉ ያስቀረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ይርጋለም ተሾመ በበኩላቸው፣ የዲጂታል መሶብ አገልግሎት አሰጣጥ እጅግ የተራቀቀና ቅልጥፍና የተሞላበት በመሆኑ ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ መነሻ የሚሆን ነው ብለዋል። ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር በአጠቃላይ በሀገሪቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠውና ለቀጣዩ ትውልድ መልካም አሻራ የሚጥል መሆኑንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አስቻለው አድማሱ፣ የመሶብ አገልግሎት ቀደም ሲል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበሩ በርካታና ውስብስብ ችግሮችን ያስወገደ መሆኑን ተናግረዋል። ይህ ዘመናዊ የዲጂታል አሰራር በግለሰብ ደረጃ ምቾትን ከመፍጠሩ ባለፈ፣ እንደ ሀገርም ትልቅ እድገትና እምርታ መሆኑን በተጨባጭ ማረጋገጡን አስረድተዋል። አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል መሰጠታቸው አላስፈላጊ መጉላላቶችን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስ የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ነዋሪ አቶ ብርሃን አብርሃ ናቸው። አቶ ብርሃን ከዚህ ቀደም የነበረው አሰራር እጅግ አድካሚና ውጣ ውረድ የበዛበት እንደነበር አስታውሰው፣ የአሁኑ ግን የተቀላጠፈና ምቹ መሆኑን መስክረዋል።
የኢጋድ የሳይበር የተግባር ልምምድ የአባል ሀገራትን የጋራ ደህንነት ለማረጋገጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል ፈጥሯል
Jun 30, 2026 1353
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የኢጋድ የሳይበር የተግባር ልምምድ የአባል ሀገራትን የጋራ ደህንነት ለማረጋገጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል እንደፈጠረላቸው አስተያየታቸውን የሰጡ የስልጠናው ተሳታፊ ሀገራት ተወካዮች ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሣ) ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢጋድ ቀጣናዊ የሳይበር የተግባር ልምምድ ሥልጠና ላለፋት አምስት ቀናት በአዲስ አበባ ተሰጥቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና የጅቡቲ ተወካዮች ተሳትፈዋል። በጅቡቲ የሚገኘው የኢጋድ ዋና መሥሪያ ቤት የሳይበር ደህንነት እና የዳታ አስተዳደር ከፍተኛ ባለሙያ ኸድራ አሊ ዩሱፍ እንደገለጹት፤ ሥልጠናው ከፖሊሲ ቀረጻ ጀምሮ እስከ ቴክኒካዊ ልምምድ ድረስ ያሉ በርካታ ዘርፎችን ያካተተ ነበር ብለዋል። በተለይም የሳይበር ደህንነት ሥጋት መረጃ ትንተና እና የማልዌር ወይም የጎጂ ሶፍትዌሮች ምርመራ ላይ ሰፊ ትኩረት መደረጉን አመልክተዋል። የሳይበር ሥጋቶችና ጥቃቶች በተፈጥሮ ድንበር ተሻጋሪ በመሆናቸው መርሃ ግብሩ በአባል አገራቱ መካከል ያለውን የጋራ የመከላከል አቅም እና ቀጣናዊ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በኡጋንዳ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ውስጥ ዋና የሲስተምስ አድሚኒስትሬተር ሮበርት ልዋሳ እንደተናገሩት፤ መርሃ ግብሩ እንደ ኢትዮጵያና ዩጋንዳ ያሉ የኢጋድ አባል አገራት የሳይበር ደኅንነትን እንዴት እየተገበሩት እንደሆነና ያላቸውን የአስተዳደር መዋቅር እርስ በእርስ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው ብለዋል። የሳይበር ጥቃት ድንበር ተሻጋሪና ዓለም አቀፋዊ ሥጋት መሆኑን በመጥቀስ ጥቃቶቹን ለመቋቋም ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታና አብሮ መስራት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በደቡብ ሱዳን የብሔራዊ የሳይበር ደህንነት ቁጥጥር ማዕከል አናሊስት ዮም ማሉአል ማጆክ በበኩላቸው፤ ሥልጠናው ሙሉ በሙሉ በተግባር እና በእውነተኛው ዓለም ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የሳይበር ጥቃቶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በየአገራቱ የሚገኙ የመንግሥት መሠረተ ልማቶችን፣ የፋይናንስ ሥርዓቶችን እና የግል ተቋማትን ከጥቃት ለመጠበቅ የትኞቹ ሰርቨሮችና ሥርዓቶች ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ትልቅ ግንዛቤ ያገኘንበት ነው ብላለች። ወደ አገራቸው ሲመለሱም ይህንን ተግባራዊ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። የሶማሊያ ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኮምፒውተርና መረጃ ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን መሐመድ በበኩላቸው ሥልጠናው እጅግ አስደናቂና ከፍተኛ እውቀት የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ በሳይበር ደኅንነት ዘርፍ ያላትን ልምድና ያሳየችውን ዕድገት ማጋራቷ ለአባል አገራቱ ጠቃሚ መሆኑን ጠቁመዋል። ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎችም ሰፊ እውቀትና ልምድ ማግኘታቸውን በመግለጽ ተሳታፊዎቹ በሥልጠናው መደሰታቸውን አክለዋል።
ስፖርት
ሞሮኮ ካናዳን 3ለ0 በመርታት በዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆነች
Jul 4, 2026 112
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ሞሮኮ ካናዳን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በሂውስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የ26 ዓመቱ የአማካይ ተጫዋች አዜዲን ኡናሂ በ50ኛው ፤ በ82ኛው እና ሶፊያን ራሒሚ በጭማሪ ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥሯል። የሰሜን አፍሪካዋ ሞሮኮ በመጀመሪያው አጋማሽ ብልጫ ቢወሰድባትም በሁለተኛው 45 የተሻለ እንቅስቃሴ አድርጋለች። የሞሮኮው ወሳኝ ተጫዋች ኢስማኤል ሳይባሪ (አጥቂ) ባጋጠመው የጡንቻ ጉዳት ምክንያት በ22ኛው ደቂቃ በሶፊያን ራሂሚ ተቀይሮ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ሞሮኮ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለች የመጀመሪያ ሀገር ሆናለች። በሩብ ፍጻሜው ከፓራጓይ እና ፈረንሳይ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ኳታር እ.አ.አ በ2022 በተካሄደው 22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮ ግማሽ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያ አፍሪካዊ ሀገር በመሆን ታሪክ መስራቷ ይታወቃል። የአትላስ አንበሶች በዘንድሮውም የዓለም ዋንጫ በስኬታማ ጉዟቸው ቀጥለዋል። ከዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ካናዳ ጉዞዋ 16 ውስጥ ተገቷል። በሌላኛው የ16ቱ ጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ፓራጓይ ከፈረንሳይ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ላይ በፊላደልፊያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በዛምቢያ አቻው ተሸነፈ
Jul 4, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27 /2018 (ኢዜአ)፦ በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ኢትዮጵያ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ ዛምቢያ ኢትዮጵያን 2 ለ 1 አሸንፋለች። በንዶላ ሌቪ ምዋናዋሳ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍሪዳ ንዳሼ እና ፒዳ ሙዙዋ የዛምቢያን ጎሎች አስቆጥረዋል። ምኅረት አየለ የኢትዮጵያን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ኢትዮጵያ ከሜዳዋ ውጪ ግብ ማስቆጠሯ በመልሱ ጨዋታ ውጤቱን ለመቀልበስ ተስፋ የሚሰጥ ነው። የሁለቱ ሀገራት የመልስ ጨዋታ ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይካሄዳል። ኢትዮጵያ በድምር ውጤት ካሸነፈች በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለፊፋ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ማለፏን ታረጋግጣለች። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ 24 ሀገራት ይሳተፋሉ። በዓለም ዋንጫው አፍሪካ ሞሮኮን ጨምሮ በአምስት ሀገራት ትወከላለች። ቀሪ አራት ሀገራት በመጨረሻው ዙር የማጣሪያ ጨዋታዎች ይለያሉ።
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ከዛምቢያ ጋር ይጫወታል
Jul 4, 2026 269
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27 /2018 (ኢዜአ)፦ በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ኢትዮጵያ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ዛሬ ከዛምቢያ ጋር ታደርጋለች። ጨዋታው ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በንዶላ ሌቪ ምዋናዋሳ ስታዲየም ይካሄዳል። በአሰልጣኝ ራውዳ አሊ የሚመራው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያ ዙር ደቡብ ሱዳንን በድምር ውጤት 8 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል። በሁለተኛው ዙር ኢትዮጵያ ብሩንዲን በአጠቃላይ ውጤት 4 ለ 2 በማሸነፍ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። በካሮል ካኒዬምባ የሚሰለጥነው የዛምቢያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያ ዙር ሩዋንዳን በደርሶ መልስ ውጤት 4 ለ 1 አሸንፋለች። ዛምቢያ በሁለተኛው ዙር ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክን በድምር ውጤት 7 ለ 0 በመርታት ለወሳኙ ጨዋታ ደርሷል። አሰልጣኝ ራውዳ ዓሊ ከዛምቢያ ጋር ለሚደረገው ጨዋታ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ ማድረጓ ይታወቃል። ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ከሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ዝግጅታቸውን ሲያደርጉ ቆይተዋል። ብሔራዊ ቡድኑ ለጨዋታው በሳምንቱ አጋማሽ ወደ ዛምቢያ አቅንቷል። ለዛሬው ጨዋታ የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት በንዶላ ሌቪ ምዋናዋሳ ስታዲየም አከናውኗል። ተጫዋቾቹ በሙሉ ጤንነት እና በጥሩ ሞራል ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ካሮል ካኒዬምባ ዛምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ላለባት ጨዋታ ለ35 ተጫዋቾች የመጀመሪያ ጥሪ ያደረገች ሲሆን በመጨረሻ ስብስቡ የተቀነሰ ተጫዋች የለም። የሁለቱ ሀገራት የመልስ ጨዋታ ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ኢትዮጵያ በድምር ውጤት ካሸነፈች በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለፊፋ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ማለፏን ታረጋግጣለች። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ 24 ሀገራት ይሳተፋሉ። በዓለም ዋንጫው አፍሪካ ሞሮኮን ጨምሮ በአምስት ሀገራት ትወከላለች። ቀሪ አራት ሀገራት በመጨረሻው ዙር የማጣሪያ ጨዋታዎች ይለያሉ።
ሞሮኮ ወደ ሩብ ፍጻሜ ለመግባት ካናዳ ጋር የምታደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Jul 4, 2026 367
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል። ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ ካናዳ ከሞሮኮ በሂውስተን ስታዲየም ይጫወታሉ። ካናዳ በ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ደቡብ አፍሪካን 1 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፋለች። የሰሜን አሜሪካዋ ሀገር በዓለም ዋንጫው 16 ውስጥ ስትገባ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ሞሮኮ ኔዘርላንድስን በመርታት ሌላኛው የጥሎ ማለፍ ምዕራፍ ተሸጋግራለች። በጨዋታው ሞሮኮ በ120 ደቂቃ አንድ አቻ የተለያየች ሲሆን በመለያ ምት ተጋጣሚዋን 3 ለ 2 ረትታለች። የአትላንስ አንበሶቹ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪካቸው 16 ውስጥ ሲገቡ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ነው። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ከዚህ ቀደም አንድ ጊዜ ተገናኝተዋል። ኳታር ከአራት ዓመት በፊት ባዘጋጀችው 22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በምድብ መርሐ ግብር ተገናኝተው ሞሮኮ 2 ለ 1 ማሸነፏ አይዘነጋም። ሞሮኮ በወቅቱ እስከ ግማሽ ፍጻሜ ድረስ ድንቅ ግስጋሴ በማድረግ በዓለም ዋንጫ ታሪክ የመጨረሻ አራት ውስጥ የገባች የመጀመሪያ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ብሔራዊ ቡድኖቹ እስከ አሁን ባደረጓቸው አራት ጨዋታዎች ሞሮኮ ሶስቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ይዛለች። በቀሪው አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። ሞሮኮ የማሸነፉን የቅድሚያ ግምት ወስዳለች። የሁለቱ ሀገራት አሸናፊ ከፓራጓይ እና ፈረንሳይ አሸናፊ ጋር በሩብ ፍጻሜው ይገናኛል። በሌላኛው መርሐ ግብር ፓራጓይ ከፈረንሳይ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ላይ በፊላደልፊያ ስታዲየም ይጫወታሉ። ፓራጓይ በ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ሳትጠበቅ የአራት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋን ጀርመንን በማሸነፍ 16 ወስጥ ገብታለች። የደቡብ አሜሪካዋ ሀገር በ120 ደቂቃ አንድ አቻ የወጣች ሲሆን በመለያ ምት 4 ለ 3 በማሸነፍ በዘንድሮው ዓለም ዋንጫ ማንም ያልገመተውን ውጤት አስመዝግባለች። ፓራጓይ 16 ውስጥ ስትገባ የአሁኑ ለአምስተኛ ጊዜ ነው። የሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ፈረንሳይ ስዊድንን በበማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅላለች። የዘንድሮውን ዓለም ዋንጫ የማንሳት ሰፊ ግምት ያገኘችው ፈረንሳይ ለሰባተኛ ጊዜ ወደ 16ት ውስጥ ገብታለች። ፈረንሳይ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ 16 ውስጥ ተሸንፋ አታውቅም። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም በዓለም ዋንጫው ሁለት ጊዜ ተገናኝተው ፈረንሳይ ጨዋታዎቹን በድል ተወጥታለች። ፈረንሳይ እ.አ.አ በ1998 ባዘጋጀችው 16ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ 16 ውሰጥ ተገናኝተው አዘጋጇ ሀገር 1 ለ 0 ያሸነፈች ሲሆን እስከ መጨረሻው በመሄድ የመጀመሪያ ዋንጫዋን አንስታለች። ስዊድን እ.አ.አ በ1958 ባዘጋጀችው ስድስተኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በምድብ ሁለት ተገናኝተው ፈረንሳይ 7 ለ 3 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነበት አሸንፋለች። በዛሬው የሁለቱ ሀገራት ጨዋታ ፈረንሳይ የማሸነፉን ሰፊ የቅድሚያ ግምት ወስዳለች።
አካባቢ ጥበቃ
የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ልዑካን በታሪካዊቷ ላሊበላ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ
Jul 4, 2026 175
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ልዑካን ቡድን አባላት በታሪካዊቷ ላሊበላ ከተማ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች፣ በዩኔስኮ በተመዘገበው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ቅጥር ግቢ ነው የአረንጓዴ ዐሻራቸውን ያኖሩት። በታሪካዊቷ የላሊበላ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኘው የዲፕሎማቲክ ልዑክ፣ ትናንት የዓለም ድንቅ ቅርስ የሆነውን የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በተጓዳኝም በዛሬው ዕለት በቅርስ መዳረሻው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ቅጥር ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሂደዋል። የልዑካኑ የችግኝ ተከላ የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከቅርስና አካባቢ ጥበቃ ጋር በአርዓያነት ተሰናስሎ የሚሰራበት መሆኑን ዓለም አቀፋዊ የልማት አጀንዳ መሆኑ ተገልጿል። ጉብኝቱና የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያን ጥንታዊነት፣ አስደናቂ የኪነ-ሕንጻ ጥበብና የባህል ዕሴቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይበልጥ ለማስተዋወቅ ትልቅ አጋጣሚን ፈጥሯል። ጉብኝቱም ኢትዮጵያ ለቱሪስቶች አስተማማኝና ማራኪ መዳረሻ መሆኗን ለዓለም በመገለጥ የቱሪዝም ዘርፍ ለማነቃቃት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል። የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ተወካዮች በቅርስ ስፍራው ችግኝ መትከላቸው፣ የዓለም ቅርሶችን የመንከባከብና የአየር ንብረት ለውጥን በጋራ የመከላከል ዓለም አቀፋዊ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። የዲፕሎማቶች ጉብኝትና የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን በመጠቀም ለመልካም ገጽታ ግንባታና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ለምታደርገው ጥረት አጋዥ ሚና ይኖረዋል።
ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ስትራቴጂካዊ ፕሮግራሞችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበች ነው -ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)
Jul 4, 2026 385
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ስትራቴጂያዊ ፖሊሲዎችንና ፕሮግራሞችን በውጤታማነት በመተግበር ተጨባጭ ውጤት እያመጣች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፅም አሰፋ (ዶ/ር) ገለፁ። ለመጪው ትውልድ ጽዱ፣ ጤናማና አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ የተጀመረው የ"ጽዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ" ሦስተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደተናገሩት ሦስተኛው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ባለፉት ሁለት ዙሮች የተገኙ ውጤቶችን በማስፋት ለሀገሪቱ ዘላቂ ልማትና አካባቢ ጥበቃ ወሳኝ አቅም የሚፈጥር ነው። ንቅናቄው ለዜጎች ጤናማና ንጹህ አካባቢ ለመፍጠር እና ለመጪው ትውልድ ፅዱ ኢትዮጵያን ለማውረስ የጋራ ቁርጠኝነትን ማረጋገጫ ነው ብለዋል። የከተሞች መስፋፋት፣ የፕላስቲክ ቆሻሻ መጨመር፣ የአደገኛ ኬሚካሎችና ቆሻሻዎች ተገቢ አያያዝ እጥረት፣ የድምፅ ብክለት እና ሌሎች የአካባቢ ችግሮች የዜጎችን ጤና፣ የአካባቢን ደህንነትና የዘላቂ ልማት ጉዞአችንን እየተፈታተኑ እንደሚገኙም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ በርካታ ስትራቴጂያዊ ፖሊሲዎችንና ፕሮግራሞችን እየተገበረ ይገኛል ብለዋል። የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ፣ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ፣ የንፁህ ኃይል ሽግግር፣ የከተማ ኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች፣ አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ከረጢቶችን የሚከለክል ሕግ፣ እንዲሁም የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን ከውጭ የማስገባት ክልከላ የዚህ ቁርጠኝነት ተጨባጭ ማሳያዎች መሆናቸውን አብራርተዋል። በመርሃ ግብሮቹ ትግበራም ተጨባጭ ውጤት መምጣቱን አንስተዋል። ሀገሪቱ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች እየወሰደቻቸው ያሉ የመፍትሔ እርምጃዎችና ያላት ቁርጠኝነት በዓለም አቀፍና በአህጉር ደረጃ ያላትን ተሰሚነት ከፍ ያደረገ መሆኑንም ገልፀዋል። በተለይ የአየር ንብረት ለውጥን በዘላቂነት ለመከላከል እንደሀገር በየዓመቱ እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከፍተኛ ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል። በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን መሪነት እየተተገበረ የሚገኘው የፅዱ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ንቅናቄ ንፁህና ጤናማ አካባቢ ለመፍጠር እየተከናወኑ ካሉ ዓበይት ተግባራት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። የአካባቢ ጥበቃ ተቋማዊ ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግም የተለያዩ ህግጋት ወደ ተግባር መግባታቸውን ተናግረዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ሁለት ዙሮች የተካሄዱ የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄዎች ለአካባቢ ጥበቃ ውጤታማ ተግባራት የተከናወነባቸው መሆናቸውን ተናግረዋል። በመጀመሪያው ዙር ከ15 ሚሊየን በላይ በሁለተኛው ዙር ደግሞ ከ54 ሚሊየን በላይ ህዝብ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ዘዴዎች ተደራሽ በማድረግ በባለቤትነት እንዲሳተፉ መደረጉን አንስተዋል። 3ኛው ዙር ንቅናቄ የፕላስቲክ ብክለት፣ የአደገኛ ኬሚካሎችንና አደገኛ ቆሻሻዎችን መከላከል እንዲሁም የድምፅ ብክለትን መከላከል ላይ ያተኮረ መሆኑን ጠቅሰዋል። የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ለአካባቢ ጥበቃ መሰረት እየጣለ መሆኑን ገልጸው፥ ለስኬታማነቱ ጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎና የጋራ ቁርጠኝነትን እንደሚጠይቅ አስረድተዋል።
የአካባቢ ብክለትን መከላከል ከሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጋር የተሳሰረ ብሔራዊ የልማትና ደኅንነት ጉዳይ ነው
Jul 4, 2026 350
የአካባቢ ብክለትን መከላከል ከሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጋር የተሳሰረ ብሔራዊ የልማትና ደኅንነት ጉዳይ ነው አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአካባቢ ብክለትን መከላከልና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ከኢኮኖሚ ምርታማነትና ከሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጋር የተሳሰሩ ብሔራዊ የልማትና ደኅንነት ጉዳዮች መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ። ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃና በአረንጓዴ ልማት ለአፍሪካ ተምሳሌት ሀገር መሆን መቻሏንም ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 3ኛውን ዙር የ"ጽዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ" ሀገር አቀፍ ንቅናቄ በይፋ አስጀምረዋል። በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክትም፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት በመላ ሀገሪቱ በመደመር መንግሥት እየተተገበረ ያለው የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ልማት ከተሞችን ጽዱ፣ አረንጓዴ፣ ውብ እንዲሁም ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረጉም ባሻገር፣ የቱሪስት መስሕብነታቸውን እያሳደገው መሆኑን ተናግረዋል። ሦስተኛው ዙር የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄም ከእነዚህ ሀገራዊ መርሃ ግብሮች ጋር በተቀናጀ መልኩ እንደሚተገበር ገልጸዋል። የፕላስቲክ ብክለት፣ የአደገኛ ቆሻሻዎች አያያዝ እና የድምፅ ብክለት ለአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ብቻ ሳይሆኑ ከሕዝብ ጤና፣ ከኢኮኖሚ ምርታማነት፣ ከኢንቨስትመንትና ከሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጋር የተሳሰሩ ብሔራዊ የልማትና ደኅንነት ጉዳዮች መሆናቸውን አስገንዝበዋል። እነዚህን ተግዳሮቶች መፍታት የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገራችንን ዘላቂ ልማት፣ ተወዳዳሪነት እና የትውልዶችን የወደፊት ዕድል የሚወስን ሀገራዊ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነውም ብለዋል። ባለፉት ሁለት ዙሮች የተካሄዱት የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄዎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የተሳተፉባቸውና ትልልቅ ስኬቶች የተመዘገቡባቸው መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ሦስተኛው ዙር ንቅናቄም የቀደሙትን ጠንካራ ጎኖች በማጠናከር እንዲሁም የክትትል፣ የሪፖርት ሥርዓት እና የተቋማዊ ቅንጅት ክፍተቶችን በጥልቀት በመገምገም መዘጋጀቱን አስረድተዋል። ንቅናቄው በግንዛቤ ፈጠራ ላይ ብቻ ሳይወሰን በሚለኩ ውጤቶች፣ በጠንካራ ክትትልና ግምገማ እንዲሁም በተቋማዊ ተጠያቂነት ላይ በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቀዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በብክለት መከላከል፣ በአካባቢ ጥበቃና ተያያዥነት ባላቸው ሕጎች ዝርጋታና ተፈጻሚነት እንዲሁም በኅብረተሰብ ግንዛቤ ፈጠራ ላይ ተምሳሌታዊ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። የንቅናቄውን ስኬታማነት ለማረጋገጥ ሁሉም የክልል መንግሥታትና የከተማ አስተዳደሮች እንደየአካባቢያቸው ሁኔታ ግልጽ የትግበራ ዕቅድ በማዘጋጀት፣ በጀት በመመደብና ጠንካራ የክትትልና ሪፖርት ሥርዓት በመዘርጋት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል። በተለይም የክልል ፕሬዚዳንቶች፣ ከንቲባዎችና የአካባቢ ጥበቃ ተቋማት አመራሮች የመሪነት ኃላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ለሀገራዊ ንቅናቄው መሳካት የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማኅበራት፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሴቶችና ወጣቶች በአንድነት እንዲንቀሳቀሱም ጠይቀዋል። መጪው ትውልድ የሚረከባት ኢትዮጵያ ከሙስና፣ ከአድልዎና ከብልሹ አሠራር ብሎም ከአካባቢ ብክለት የጸዳች እንድትሆን የጋራ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የተጀመረው ጉዞ ለጽዱ አካባቢ፣ ለጤናማ ማኅበረሰብ፣ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ እና ለተሻለች ኢትዮጵያ የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለመጪው ትውልድ የምናስተላልፈው ትልቁ ቅርስ ጽዱ፣ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ዘላቂ ኢትዮጵያ መሆን አለበት ብለዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር የአደጋ ቅድመ መከላከል ውጤታማነትን እያጎለበተ ነው
Jul 4, 2026 207
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተሞችን ውበት በማጎናጸፍ የአደጋ ቅድመ መከላከል ውጤታማነትን እያጎለበተ መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አመራር፣ ሠራተኞችና ባለድርሻ አካላት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል አካባቢ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በመርሃ ግብሩ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ቢሊዮን ችግኞችን መትከል ያስቻለ ስኬታማ የልማት ንቅናቄ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ህዝቦቿን በማስተባበር በየዓመቱ በብሔራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ የምትተክላቸው ችግኞች የአካባቢ ጥበቃን በማሳደግ ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የጎርፍ፣ መሬት መንሸራተትና የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ ለአደጋ ቅድመ መከላከል ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአረንጓዴ ልማት ተምሳሌት ከተሞችን በማስፋፋትም ንጹህ አየርና ውብ ገጽታ የተላበሰ ምኅዳር እንዲፈጠር በማድረግም ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተሞችን ውበት በማጎናጸፍ የአደጋ ቅድመ መከላከል ውጤታማነትን እያጎለበተ ነውም ብለዋል፡፡ አዲስ አበባም የአረንጓዴ ውበት ምሳሌ ሆናለች ያሉት ኢንጂነር ወንድሙ፤ በቀጣይም ማህበረሰቡ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተለመደውን ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል። የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር አሕመድ መሐመድ በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የአካባቢ ልማት ብቻ ሳይሆን የቅድመ አደጋ መከላከል ሥራ ነው ብለዋል። በዚህም ባለድርሻ አካላት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ የጎርፍና ተያያዥ አደጋዎችን ቀድሞ መከላከል እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 16068
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 10746
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 9553
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 9452
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች
Jun 29, 2026 3002
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • ምንድንነት የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም ‘አስም’ እንደሚባልም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የኪንታሮት ህመም እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? • ምልክቶች የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ጠቁመዋል። ምልክቶቹም በአብዛኛው በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ አስገንዝበዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር)፣ የእንስሳት አይነ ምድር ሽታዎች ለዚህኛው አስም አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን አስረድተዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑንም ተናግረዋል። • አጋላጭ (ለህመሙ መባባስ) መንስዔዎች አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የዓየር ብክለት፣ ጭስ)፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ዓይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? 👉ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎችዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ 👉 በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ 👉 በቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ ሙቀት የሚሰጡ መከላከያ ልብሶችን መልበስ፤ 👉 ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ • ሕክምናው የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የዓየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ከ 3 እስከ 10 በመቶ ያህሉ የዓለም ሕዝብ በአስም ተጠቂ መሆኑንም ጠቁመዋል። #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢዜአ #የጤና_ነገር
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 2800
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ከተጽዕኖ ፈጣሪነትና ተደማጭነት መጎልበት እስከ የአኅጉር ድምጽ መሆን - የኢትዮጵያን ታላቅነት የገለጠው የዲፕሎማሲው ዘርፍ ስኬት
Jun 25, 2026 3479
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቷ የፓን አፍካኒዝም ንቅናቄን በማንሳት አኅጉራዊ ተቋማት እንዲመሠረቱ ፊታውራሪ ከመሆን ጀምሮ ለጎረቤቶቿ ሰላም ጉልኅ ሚና ተጫውታለች፤ አሁንም ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔን እያሰረጸች በርካቶች እንዲጋሯት አድርጋለች። እንደ ሀገር ከለውጡ መንግሥት ወዲህ ከተገኙ በርካታ ትላልቅ ስኬቶች መካከል በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው አንዱ ነው። ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የለውጡ መንግሥት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ዋነኛ መለኪያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ነው። የኢትዮጵያ ሁኔታዎችን የማሰብ፣ የመፈለግና የመከወን ሂደት ንጥል (ለራስ ብቻ የሚል) ሳይሆን፤ በወንድማማችነት/እህትማማችነት ዕሳቤ በጋራ ማደግን ያነገበ ነው። ይህ ሂደቷም በበርካታ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ እንዲሁም አኅጉር አቀፍ ተቋማት ተወድሷል። በዚህም ሐሳቦቿ ቅቡል ሲሆኑ ተመልክተናል። ኢትዮጵያ የ#BRICS አባል መሆን መቻሏ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ይህም ተሰሚነቷን ያረጋገጠ ማስረጃ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ተያያዥ ጉዳዮች ዘርፈ-ብዙ ጥቅም በማስገኘት የበለጸገች ኢትየጵያን ዕውን የማድረግ ጉዞው ያፋጥናል። ወዲህ ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልና አፍሪካን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና መመረጧም የአኅጉሪቱ ድምጽ መሆኗን ይነግረናል። ዓለም አቀፍ ብሎም አኅጉር አቀፍ የሆኑ በርካታ ኮንፈረንሶችም በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እንዲካሄዱ መደረጉ አንድምታው ብዙ ነው። በብቃት ማስተናገዷ ደግሞ ሌላኛው ጥንካሬዋ። ሌላው የሀገራችንን የተጨበጠ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት የሚገልጽልን፤ የዓለም የዓየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን (COP32) እንድታዘጋጅ መመረጧ ነው። ይህን ትልቅ ዕድል በርካቶች ስለተመኙት አላገኙትም፤ ኢትዮጵያ ግን ዜጎቿን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባከናወነችው ያላሰለሰ ትጋት አግኝታዋለች። ግጭት ባለባቸው የቀጣናው ሀገራትም በመንግሥታቱ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት ሥር ከምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባለፈ፤ በግሏ የሰራችው ብዙ ነው። ከራሷ አልፋ ለጎረቤቶቿ ዘብ መሆኗ፤ በአብሮነት መኖርን እና በጋራ ማደግን በተግባር የገለጠች ሀገርም ያደርጋታል። ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ በሚለው ቅድሚያ ለሀገር በቀል ዕውቀቶች በሩን ክፍት ባደረገው ትጋቷም፤ በበርካታ የአኅጉሪቱ ሀገራት ዘንድ ምሥጋና አስችሯታል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲዋም በተለያዩ ሀገራት በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎቿን ከሀገራቱ እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመነጋገር በተሳካ ሁኔታ ልጆቿን ወደ ዕቅፏ መልሳለች፤ በቅርቡ በሳዑዲ ዓረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምኅረት ዐዋጅ እንዲሰጣቸው መደረጉ አንድ ማሳያ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን ጨምሮ በተለያዩ አኅጉራት በሚገኙ ሀገራት መሪዎችና ተወካዮች ዘንድ በስፋት የተመረጠችና የተጎበኘች ሀገር መሆኗን ማስታወስ ተገቢ ነው። ከጉብኝት ባለፈ ትላልቅ ስምምነቶችም የተፈራረመች መሆኗን ልብ ማለት ይገባል፤ ይህም የምታነሳውን ሐሳብ ገዥነትና የአፍሪካ መግቢያ በር መሆኗን ያሳያል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ መሆኑን መረዳት ይገባል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድርድር ሂደት የተጎናጸፈችው የዲፕሎማሲ ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መነቃቃት መፍጠሩንም ማጤን ያስፈልጋል። ይህ የተሳካው ሀገሪቱ ኢትዮጵያ መንገዷም የጋራ ልማትን የሰነቀ ዕውነት በመሆኑ ነው። በቀጣይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለአንዲት ሀገራቸው አምባሳደር በመሆን፤ የዲፕሎማሲውን ሥራ በይበልጥ ማገዝ ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ካልሠሩ ማን ለሀገራቸው ሊሠራ ይችላል?
እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል?
Jun 25, 2026 2669
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በዝምታ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት፤ የጨጓራ፣ አንጀትና ጉበት ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሚፍታህ ደሊል ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የጉበት ጤናን እንዴት መጠበቅ እንደሚቻል፣ ለጉበት ጤና መታወክ ስለሚያጋልጡ ጉዳዮች፣ ስለጉበት ስብ (ቅባት) እንዲሁም ሕክምናው ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል። · በሰው ልጅ ሕይዎት (ሠርካዊ እንቅስቃሴ) ውስጥ የጉበት ሚና ምንድን ነው? ዶክተር ሚፍታህ እንደገለጹት፤ ጉበት በሰውነታችን ውስጥ ኪሚገኙ ትላልቅ የውስጥ አካል ክፍሎች (ኦርጋኖች) አንዱ ነው። ከ1 ሺህ በላይ ተግባራትን የሚያከናውን ትልቁ እና ባተሌ የሆነ የአካል ክፍል መሆኑንም አስረድተዋል። የኪንታሮት በሽታ መንስዔ ይታወቃል? ካንሰር እንዴት ይከሰታል? · ለጉበት ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ይታወቃሉ? ለጉበት ህመም አጋላጭ ከሆኑ መንስዔዎች መካከል፤ ቫይረሶች (ሄፓታይትስ ቢ፣ ሄፓታይትስ ሲ) እንዲሁም አልኮል (ከፍተኛ መጠን ያለው አልኮል መጠጣት) መሆናቸውን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅት ደግሞ በስፋት የሚስተዋለው አጋላጭ መንስዔ የጉበት ስብ መጨመር መሆኑንም በአጽንዖት ገልጸዋል። በእኛ ሀገር ደረጃ ከሚከሰቱ የጉበት ህመሞች 50 በመቶው በሄፓታይትስ ቢ ምክንያት የሚከሰት ነው ይላሉ ዶክተር ሚፍታህ። ከ15 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የጉበት ህመም የሚከሰተው ደግሞ በአልኮል ምክንያት መሆኑን ነው ያስረዱት። እንዲሁም በሄፓታይትስ ሲ ምክንያት የሚከሰተው የጉበት ህመም ከላይ ከተገለጹት ቀጥሎ በሦስተኛነት እንደሚቀመጥም አመላክተዋል። አሁን አሁን ደግሞ ይላሉ ዶክተር ሚፍታህ፤ በሥራም ሆነ ለመዝናናት ለረጂም ሠዓታት መቀመጥን ተከትሎ የጉበት ስብ (ቅባት) በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋና ለጉበት ህመም እያጋለጠ መሆኑን አስገንዝበዋል። · የጉበት ፋት (ስብ፣ ቅባት) ለጉበት ህመም የሚያጋልጥበት ምክንያት ምንድን ነው? የጉበት ስብ በተለያዩ ሀገራት (በእኛም ሀገር በትላልቅ ከተሞች) በስፋት የሚከሰት ነው ያሉት ዶክተር ሚፍታህ፤ የጥናት ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከዓለም ሕዝብ 30 በመቶው (1/3ኛው ወይም ከ2 ቢሊየን በላይ ያህሉ) የጉበት ስብ ሊኖርበት ይችላል ይላሉ። በእርግጥ ሁሉም የጉበት ስብ ወደ ከፍተኛ የጉበት ቁስለት ይሸጋገራል ማለት እንዳልሆነ ገልጸው፤ የጉበት ስብ ካለባቸው መካከል ከ10 እስከ 15 በመቶ ያህሉ ብቻ ስቡ ከመብዛቱ የተነሳ ጉበቱን ማቁሰል እንደሚጀምር አስገንዝበዋል። ይህ ቁስለት ደግሞ እየዳነ እንደገና እያገረሸ ጠባሳ እየፈጠረ ይሄድና ጉበት ሥራውን ማከናወን የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ የጉበት መድከም ይከሰታል፤ ሰዎችም ጉዳት ይደርስባቸዋል ይላሉ። የጉበት ስብ መንስዔም፤ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ አለማድረግ (መቀመጥን ማዘውተር)፣ ፋስት ፉድ ማዘውተር (የተጠበሱ ምግቦች፣ በርገር፣ ችብስ፣ ዘይት የበዛባቸው ምግቦች) እንዲሁም ከፍተኛ ስኳር ያላቸው ለስላሳ መጠጦች፣ አልኮል መሆናቸውን አብራርተዋል። · የጉበት ስብን እንዴት መከላከል ይቻላል? የጉበት ስብ ከፍ እያለ ሲሄድ በአልትራሳውንድ እንደሚታይ (ትንሽ ከሆነ አይታም) የገለጹት ዶክተር ሚፍታህ፤ እስካሁን ክትባት እንደሌለው አረጋግጠዋል። ይህ ኬዝ እንቅስቃሴ ባለማድረግ፣ ኮምፒውተርም ሆነ ቴሌቪዥን ለማየት ረጂም ሠዓት በመቀመጥና በውፍረት መጨመር የሚከሰት መሆኑን ጠቁመው፤ መከላከያ መንገዱም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ (ቢያንስ በሳምንት እስከ 150 ደቂቃ በእግር መሄድ (ዎክ ማድረግ) ወይም በቀን ለ30 ደቂቃ ዎክ ማድረግ) መሆናቸውን ዘርዝረዋል። በተጨማሪም በፋብሪካ ፕሮሰስ የተደረጉ የታሸጉ ምግቦችን አለማዘውተር፣ ከስኳር ነጻ የሚሉ የሚበሉም ሆነ የሚጠጡ ነገሮችም ቢሆኑ በቀጥታም ባይሆን በሌላ መንገድ ጣፋጭ ስለሚኖራቸው አለማዘውተር፣ የተጠበሱ እንደ ችብስ እና መሰል ያሉ ምግቦችንም አለማዘውተር እንደሚገባ መክረዋል። ከልክ ያለፈ ውፍረት እንዳይኖር ማድረግም ለጉበት ስብ ተጋላጭነትን እንደሚቀንስ አስረድተዋል። · የጉበት በሽታ ምልክቶች እንደ ኬዙ ቢለያይም ጉበት 80 በመቶ ያህል ክፍሉ እስከሚጎዳ ምልክት ላያሳይ እንደሚችል ዶክተር ሚፍታህ ይገልጻሉ። 15 ወይም 10 በመቶ ጤናማ ክፍሉ ሲቀር (ከ85 በመቶ በላይ ክፍሉ በጣም ሲጎዳ) አንዳንድ ምልክቶች ሊያሳይ እንደሚችል ገልጸዋል። እነዚህ ምልክቶችም፤ ሆድ ላይ ውኃ መፍጠር (አሳይተስ)፣ ደም ማስመለስ መሆናቸውን እና በዚህ ወቅት የጉበት ንቅለ ተከላ ካልሆነ መፍትሔ እንደሌለው አንስተዋል። በአንጻሩ ግን፤ ‘አኪዩት ሄፓታይትስ’ የሚባለው ወይም አንድ ቫይረስ ጉበትን ሲያጠቃ ወዲያውኑ ሕክምና ይደረግለታል ሙሉ በሙሉም ይድናል ብለዋል።በዚህ ወቅት የሚየሳየው ምልክትም የዐይን ቢጫ መሆን፣ በቀኝ ደረት ሥር የውጋት ስሜት መኖር፣ ከፍተኛ ድካም መኖር፣ የምግብ ፍላጎት አለመኖር (ምግብ አስጠላኝ ማለት)፣ ማቅለሽለሽ እንዲሁም ማስመለስ መሆናቸውን አብራርተዋል። · የጉበት በሽታ አሳሳቢ ነው? የጉበት በሽታ በዓለም አቀፍ ደረጃም በተለያዩ ሀገራት ከ1 እስከ 10 ገዳይ (አሳሳቢ) ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል መሆኑን ዶክተር ሚፍታህ አስረድተዋል። በእኛ ሀገር ደረጃም የጉበት ካንሰር ከ3 እስከ 4 ገዳይ ተብለው ከሚጠቀሱ በሽታዎች መካከል መሆኑን ነው የጠቆሙት። በዓለም በየዓመቱ እስከ 3 ሚሊየን ሰዎች በጉበት በሽታ እንደሚሞቱ ገልጸው፤ ይህ አኃዝ አሳሳቢነቱን ያስረዳል ብለዋል። ምንም እንኳን ቀድሞ በሚወሰድ ክትባት (ለሄፓታይትስ ቢ) ከተከሰተ በኋላም በሚወሰድ መድኃኒት (ለሄፓታይትስ ሲ) አበረታች ውጤቶች ቢኖሩም፤ የጉበት ስብ (ቅባት) ግን በሀገራችንም ሆነ በዓለም ላይ በተለይም በከተማ ነዋሪዎች ዘንድ በስፋት እየተስተዋለ ያለ በመሆኑ አሳሳቢ ነው ብለዋል። · የጉበት በሽታ በተለይም በየትኞቹ የዕድሜ ክልሎች ላይ በስፋት ይከሰታል? የጉበት በሽታው ዓይነት በስፋት የሚከሰትበትን ዕድሜ እንደሚወስን ጠቁመው፤ በዚህም መሠረት ለምሳሌ፡- ሄፓታይትስ ቢ ከ30 ዓመት በታች ባሉ ሰዎች ላይ፣ ሄፓታይትስ ሲ ከ20 እስከ 40 ዓመት (አንዳንድ ጊዜ ከ40 ዓመት በላይ ባሉ ሰዎች ላይም ሊከሰት ይችላል)፣ የጉበት ስብ (ቅባት) ደግሞ ከ40 ዓመት በላይ ባሉ ሰዎች ላይ በስፋት እንደሚስተዋል ያስረዳሉ። · የጉበት በሽታን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? ዶክተር ሚፍታህ እንዳሉት የጉበት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የቻልባቸው የተለያዩ አማራጮች አሉ። ለምሳሌ፡- የሰውነት ክብደት (ውፍረት) ከልኩ እንዳያልፍ መቆጣጠር፣ ረጂም ሠዓት አለመቀመጥ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር፣ አልኮል አለመጠጣት (በቀን ከአንድ ቢራ በላይ መጠጣት ለጉበት ስብ ያጋልጣል)፣ ጣፋጭ ምግብና መጠጦችን መቀነስ (ጭራሽ አለመጠቀም ቢቻል)፣ ዘይት የበዛባቸውና የተጠባበሱ ምግቦችንም አለማዘውተር የሚሉትን አንስተዋል። በተጨማሪም በእኛ ሀገር ቀዳሚው የጉበት በሽታ ሄፓታይትስ ቢ መሆኑን በመግለጽ፤ ለዚህም ከ95 በመቶ በላይ የመከላከል ዐቅም ያለው ክትባት ስላለው ሦስት ጊዜ በመከተብ አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠዋል። · የሕክምና አማራጮች አሉት? ሄፓታይትስ ቢ ተከስቶ ጉበቱን ማቁሰል ከጀመረም የሚሰጥ ውጤታማ መድኃኒት መኖሩን አስታውቀዋል። ይህ መድኃኒት ምናልባት ዕድሜ ልክ ሊወሰድ ይችላል ነገር ግን ቁስለቱንም ሆነ ቫይረሱን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ነው ያሉት። ሄፓተይትስ ሲ ከሆነ ደግሞ በጣም ውጤታማ የሆነ ለሦስት ወር የሚሰጥ መድኃኒት አለ ብለዋል። ጠባሳ ከሆነ እና ከ85 በመቶ በላይ የሚሆነው የጉበት ክፍል ከተጎዳ (ከተበላሸ) ግን በውጭ ሀገር የጉበት ንቅለ ተከላ ማድረግ አስገዳጅ ይሆናል ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ ተላላፊ ካልሆኑ የጉበት በሽታዎች አንዱ እና አሁን በስፋት እየተስተዋለ ያለውን የጉበት ስብ (ቅባት) ጨምሮ የጉበት ጤናን ለመጠበቅ፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በየቀኑ ማድረግን መክረዋል። በዓመት አንድ ጊዜ የጤና ምርመራ በማድረግ ያሉበትን ሁኔታ ማወቅም ቢለመድ ሲሉ ይመክራሉ። በወቅቱ ከተደረሰብት የጉበት በሽታ መዳን እንደሚችል ገልጸው፤ በቸልተኝነት ወደ ተወሳሰበ ደረጃ ከፍ ካለ ግን እስከ ጉበት ካንሰር ሊደርስ እንደሚችልም አመላክተዋል።
ትንታኔዎች
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 602
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 1296
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 1390
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 5091
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 6911
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 18789
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 11846
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 17605
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 3176
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 2587
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።