ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ለማንኛውም ጥቃት ፈጣን ምላሽ ሰጪና ስጋቶችን አስቀድሞ መከላከል የሚችል የመላ ሠራዊቱ ሞዴል ኃይል ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Aug 14, 2026 137
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ) ፦ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በተለየ ወታደራዊ ጥበብ በፍጥነት ፈጣን ምላሽ ሰጪና አስቀድሞ ስጋቶችን መከላከል የሚችል የመከላከያ ዋነኛ ስትራቴጂካዊ መቺ ሀይል ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ፡፡ ኢታማዦር ሹሙ በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ውይይት ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ስለወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ለሠራዊቱ አመራሮች የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሥርዓት ለውጥ አድርጋ ገና ሳትረጋጋ ባንዳዎች ባደረሱባት ጥቃት ሀገር በተፈተነችበት ወቅት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ሠራዊት የተደቀነውን አደጋ በመቀልበስ ረገድ ከባድ የተጋድሎ አድርጓል ሲሉም በበመድረኩ ላይ ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት የውጊያ ማርሽ ቀያሪ የምድር ድሮን የሚል ስያሜ የተሰጠው ልዩ ሀይል መሆኑን በማብራራት ይህ ዕዝ አስካሁን ለሀገር ለከፈለው ዋጋ ኢትዮጵያ እንደምታከብረውና ነገም ይህንኑ ልዩ ብቃቱን ይዞ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል፡፡ ሠራዊቱ መስዋዕትነት የከፈለውና እየከፈለ የሚገኘው ሀገርን ለማሻገር መሆኑን ገልጸው፣ ይህም ሠራዊቱን ሀገርን ከውጭ ጠላት ከመከላከል ባለፈ፣ የውስጥ ሰላምን በማጽናት ህልውናችን ተጠብቆ ዕድገት እንዲቀጥል የሚያስችል የዜጎች ክብር መገለጫ አድርጎታል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው ሻዕቢያ ከጅምሩ ኢትዮጵያን ከባሕር በር ለማራቅ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር ፅምዶ ፈጥሮ ኢትዮጵያ ላይ ደባ የሰራ ሃይል መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ ሕገ-ወጡ ህወሓትም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ የሸጠና ለ27 ዓመታት ስልጣን ይዞ ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ አጠንክሮ የሰራ ቅጥረኛ የገዛ ሀገሩን ሠራዊት ያጠቃ የክህደት ሃይል ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በሕወሃት ክህደት የተፈተነች ነገር ግን ፀንታ የቆመች የልዩ ዘመቻ ሠራዊት መሰል ጠንካራ አርበኛ ልጆች ያሏት ሀገር ስለሆነች ጉዞዋን ቀጥላለች ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። ፅንፈኞቹን የጥፋት ሃይሎች በባዕዳን ስትራቴጂ ሥር ተሰልፈው ኢትዮጵያን የማዳከምና የማፍረስ ፅምዶ የተባለ ጥምረት ቀርፀው ሕዝባችንን ለስቃይና መከራ በመዳረግ ደካማ ኢትዮጵያን ለማየት ጓጉተው ቢሠሩም ይህ ፍላጎታቸው መቼም ሊሳካ አይችልም ብለዋል። ህወሃት የኢትዮጵያን ሕዝብ በመከፋፈል እርስ በርሱ እንዳይተማመን ሲሰራ የኖረ እኩይ ፖለቲካ አራማጅ ፀረ-ሀገር ሃይል ነው ብለዋል። ዛሬ ሴራው ከሽፎ የትግራይ ህዝብን ጨምሮ አጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ የዚህን መሰሪ ቡድን መጥፎ ተግባር ተርድቷል ብለዋል። አሁን ላይ ህወሃት ለሻዕቢያ እየተላላከና የቀድሞ ጠላቶቹን ጽንፈኛ ሸኔንና ፅንፈኛ ፋኖን አቅፎ የትላንት ክህደቱን በአደባባይ እየደገመው ይገኛልም ብለዋል። ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ በጀመረችው እድገትና ብልፅግና ወደፊት ትቀጥላለች፤ የታሪካዊ ጠላቶቿ ህልም አይሳካም ሲሉም ገልጸዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በአሁኑ ወቅት በትጥቅም በሰው ሀይል ግንባታ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በማስታወስ ለሰፈር ባንዳዎች ብቻ ሳይሆን በየትኛውም አቅጣጫ በሀገር ላይ ለሚቃጣ ጥቃት ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በአስተማማኝ ዝግጁነት ላይ መሆኑን ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ በማድረግ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ለውጥ ማምጣት ተችሏል
Aug 14, 2026 253
ሐዋሳ፤ ‎ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ በማድረግ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት መቻሉን የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ለወጣቶች ቀጣይነት ያለው የሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮግራም ''SEED'' በሲዳማ ክልል የሦስት ዓመት የሥራ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫ ላይ የሚመክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሄዷል፡፡   የሲዳማ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት በማብቃት በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት ተችሏል፡፡ ከዚህ ቀደም የነበረው የሥራ ዕድል ፈጠራ ክህሎት መር ባለመሆኑ የተነሳ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ውጤታማ አለመሆን የዘርፉ ፈተና ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል። ዘርፉ በዜጎች ክህሎትና አመለካከት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን እንደ ሀገር አቅጣጫ ተይዞ መሥራት ከተጀመረ በኋላ፤ በተለይ ወጣቶች በተሻለ አቅምና ፍላጎት ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡   በዚህም ውጤታማ የሆኑና ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሥራ ዕድል መፍጠር የቻሉ በርካታ ወጣቶችን ማፍራት እንደተቻለ ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ከፍተኛ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የቢሮው ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ በበኩላቸው፤ አጋር አካላትን ከሥልጠና ተቋማት ጋር በማቀናጀት የክህሎት ክፍተቶችን የመሙላት እና ወደ ሥራ የሚገቡትን የማብቃት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   ቅድሚያ ለክህሎትና አመለካከት በመስጠት የፋይናንስ፣ እንዲሁም የመሥሪያና የመሸጫ ቦታዎችን የማቅረብ ሥራ እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲቲዩት የሲዳማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የደቡብ ኢትዮጵያና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሎች አስተባባሪ አቶ ጌትነት ሳሙኤል፤ በኢንስቲትዩቱ የሚመራው የሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮግራም በአምስት ዓመታት ውስጥ ለ1 ሚሊዮን ወጣቶች ቀጣይነት ያለው የሥራ ዕድል የመፍጠር ዕቅድ አለው ብለዋል፡፡   ፕሮግራሙ ከተመረጡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ጋር በመሆን የክህሎት ሥልጠና የመስጠት፣ እንዲሁም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የብድር አቅርቦት የማመቻቸት ሥራ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡ በፕሮግራሙ በሲዳማ ክልል በሦስት ዓመታት ውስጥ ከ27 ሺህ በላይ ወጣቶች የክህሎት ሥልጠና ያገኙ ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥ ከ19 ሺህ በላይ የሚሆኑት የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው አብራርተዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመቀናጀትም ለኢንተርፕራይዞች ከ181 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር እንደተሰራጨ ጠቁመዋል፡፡   በፕሮግራሙ ድጋፍ ካገኙ ኢንተርፕራይዞች መካከል የጠይም ጋርመንት አባል የሆነችው ወጣት ቤርሳቤህ አለማየሁ እና የጃዋታ ጨርቃ ጨርቅ ማኅበር አባል የሆነችው ወጣት ራህመት ሁሴን፤ በፕሮግራሙ ባገኙት ሥልጠና ከዚህ ቀደም የነበረባቸውን የሂሳብ አያያዝና ሌሎች ክፍተቶች በመሙላት በሥራቸው ትርፋማ መሆን እንደቻሉ ገልጸዋል፡፡   በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል፡፡  
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚወስዱበት ነው
Aug 14, 2026 276
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚወስዱበት መሆኑን በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ሕብረት የሳህራዊ ሪፐብሊክ አምባሳደር ላሚን ባአሊ ገለጹ። አምባሳደር ባአሊ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በሌሎች ዘርፎች ስኬታማ ጉዞ እያደረገች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ስኬታማ ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንም አንስተዋል። ይህ ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ዜጎች የፖለቲካ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ አዎንታዊ ማረጋገጫ እንደሆነም ነው የተናገሩት። በምርጫው የፖለቲካ ፓርቲዎች በንቃት መሳተፋቸውን በመጥቀስ፣ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ውስጥ በጎ እርምጃ መሆኑንም አምባሳደር ባአሊ አስረድተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው የሪፎርም አጀንዳ በሀገሪቱ ውስጥ ለበለጠ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ልማት ዕድገት አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በተጣጣመ መልኩ የሚከናወኑ የተለያዩ የልማትና የለውጥ ሥራዎች አዎንታዊ ውጤት እያመጡ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። በሀገሪቱ እየተተገበረ ያለው የኢኮኖሚ ሪፎርም የዜጎችን ኑሮ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ጨምረው አንስተዋል፡፡ ይህ በኢትዮጵያ እውን እየሆነ ያለው ውጤታማ ሪፎርም በዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትና እውቅና ማግኘቱን ተናግረዋል። በመሆኑም ይህ የኢትዮጵያ ስኬታማ ተሞክሮ በአጠቃላይ በአፍሪካ ደረጃ የሚገኙ ሌሎች ሀገራት ትምህርት ሊወስዱበት የሚችል ነው ብለዋል። ሀገራዊ ምክክር አስፈላጊ የፖለቲካ ልምምድ እንደሆነ የጠቆሙት አምባሳደሩ፣ በኢትዮጵያ እየተደረገ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ለሁሉም አካላት ዘላቂ ጥቅም ለማስገኘት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል። በሳህራዊ ሪፐብሊክ እና በኢትዮጵያ መካከል እ.ኤ.አ ከ1970ዎቹ ጀምሮ የነበረውን ትብብር አውስተው፣ የሀገራቱ ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰዋል። ባህል፣ ስፖርት፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ጤና እና ሌሎች የጋራ ፍላጎት በሆኑ ዘርፎች የሁለትዮሽ ትብብሩን የበለጠ ለማስፋት እንደሚሰራም አምባሳደር ላሚን ባአሊ ገልጸዋል።
በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ ናቸው
Aug 14, 2026 182
አዳማ ፤ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ )፡- በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ መሆናቸውን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ገለፁ። በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የተመራ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በአዳማ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የዲጂታል መሰረተ ልማትና ሌሎች የልማት ስራዎችን ገብኝቷል።   በዚህ ወቅት አቶ ጥራቱ በየነ እንደገለጹት፤ በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ ናቸው። "ከዚህ ቀደም ልምድ ለመቅሰም ወደ ውጭ ሀገር ከተሞች እንሄድ ነበር፤ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ግን በሀገር ውስጥ ከተሞች ከቴክኖሎጂ ልማትና አጠቃቀም፣ ከአገልግሎት ዲጂታላይዜሽንና መሠረተ ልማት ዝርጋታ አንጻር ልምድና ዕውቀት መቅሰም እየቻልን ነው" ብለዋል። በተለይ በአዳማ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥን ከማዘመን እና የጸጥታና ደኅንነት አሠራሮችን ዘመናዊ ከማድረግ አኳያ የተሰሩ ሥራዎች ጥሩ ተሞክሮ የሚወሰድባቸው እንደሁኑ ገልጸዋል። በተመሳሳይም በትራንስፖርት ስምሪትና በትራፊክ ቁጥጥር ሥርዓት፣ ቴክኖሎጂን በማላመድና አገልግሎት ላይ በስፋት በማዋል ረገድ ጥሩ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።   በተለይ የመሬት ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደርና ለሕዝብ ልማት በማዋል ረገድ የአዳማ ከተማ አስተዳደር የመሬት ካዳስተር ሥርዓት በማሳያነት ሊጠቀስ የሚችል መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። በከተማ ግብርና፣ የአርሶ አደሩን ሕይወትና የአኗኗር ዘይቤ ለማዘመንና ከተማዋ አርሶ አደሩን በማቀፍ ዕድገቷ እንዲቀጥል የአርሶ አደሮች ሞዴል መንደር ልምድ የተገኘበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም አርሶ አደሩ የተሟላ መሠረተ ልማት በአንድ ቦታ እንዲያገኝ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባው አክለውም ከአዳማ ከተማ የተገኘውን ተሞክሮ በከተማቸው ካለው አተገባበር ጋር በማቀናጀት ወደ ውጤት እንደሚቀይሩትም ተናግረዋል። የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው፤ በከተማዋ በተከናወነው የመሠረተ ልማት ዝርጋታና አገልግሎትን በማዘመናችን አዳማ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንድትሆን ሰፊ ዕድል እየፈጠረ ነው ብለዋል። የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመንና በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የተገልጋዩን እርካታ ማረጋገጥ መቻሉንም ገልጸዋል። በአዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ለማዘመን የተሠራው ሥራ ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል። በዚህም የመሬት ሀብቱን በአግባቡ በማስተዳደር ከሌብነትና ምዝበራ መታደግ መቻሉን፣ የከተማዋ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን፣ ሕዝቡ በከተማዋ ልማት እያደረገ ያለው ተሳትፎ እንዲጨምርና እንዲጠናከር ማስቻሉንም ጠቁመዋል።    
በድሬዳዋ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማኅበራዊ ተቋማት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Aug 14, 2026 148
ድሬደዋ ፣ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፡-በድሬዳዋ አስተዳደር በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለትምህርት ቤቶችና ማኅበራዊ ተቋማት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተመላከተ። የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶችን ለግሷል፤ በመቄዶንያ የአረጋውያን መርጃ የድሬዳዋ ማዕከልም ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር አከናውኗል።   በወቅቱም የጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ጽጌረዳ ክፍሌ እንደተናገሩት፤ ቢሮው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከመሳተፍ ባሻገር በሁሉም የገጠርና የከተማ ወረዳዎች በሚገኙ አደባባዮች ከ30 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነዋሪዎች ነፃ ምርመራና ሕክምና እየሰጠ ይገኛል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጤናማ ማኅበረሰብን ለመፍጠርና ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በአንድነት መፍታት እንደሚቻል እያረጋገጠ መሆኑንም አስረድተዋል።   ቢሮው ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶችን የለገሰ ሲሆን፤ ለመቄዶንያ የአረጋውያን መርጃ የድሬዳዋ ማዕከልም ማዕድ ማጋራቱን ተናግረዋል። ቢሮው ከለገሳቸው የመማሪያ ቁሳቁስ በተጨማሪ ከቢሮው ሠራተኞች የተሰበሰቡ በርካታ አልባሳትን ለመቄዶንያ የድሬዳዋ ማዕከል መለገሱንም ገልጸዋል።   የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ በበኩላቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በእርስ መረዳዳትና መደጋገፍ ባህልን በማጠናከር ማኅበራዊ ችግሮችን በራስ አቅም የመፍታት ተቋማዊ አቅም ፈጥሯል ብለዋል። በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተለያዩ የሴክተርና የግል ተቋማት የተለያዩ የትምህርት መማሪያ ግብዓቶችን እየደገፉ መሆኑን አንስተዋል። ድጋፉን በማጠናከር አንድም ዕድሜው ለትምህርት የደረሰ ሕፃን ከትምህርት ገበታው እንዳይለይ በማድረግ የነገዋን ታላቅ ሀገር መገንባት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑንም አስምረውበታል። ዛሬ የጤና ቢሮ ያደረገው ድጋፍም የመረዳዳት እሴቱ መጠናከር ማሳያ መሆኑን ገልጸው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።    
የሚታይ
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ለማንኛውም ጥቃት ፈጣን ምላሽ ሰጪና ስጋቶችን አስቀድሞ መከላከል የሚችል የመላ ሠራዊቱ ሞዴል ኃይል ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Aug 14, 2026 137
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ) ፦ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በተለየ ወታደራዊ ጥበብ በፍጥነት ፈጣን ምላሽ ሰጪና አስቀድሞ ስጋቶችን መከላከል የሚችል የመከላከያ ዋነኛ ስትራቴጂካዊ መቺ ሀይል ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ፡፡ ኢታማዦር ሹሙ በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ውይይት ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ስለወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ለሠራዊቱ አመራሮች የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሥርዓት ለውጥ አድርጋ ገና ሳትረጋጋ ባንዳዎች ባደረሱባት ጥቃት ሀገር በተፈተነችበት ወቅት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ሠራዊት የተደቀነውን አደጋ በመቀልበስ ረገድ ከባድ የተጋድሎ አድርጓል ሲሉም በበመድረኩ ላይ ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት የውጊያ ማርሽ ቀያሪ የምድር ድሮን የሚል ስያሜ የተሰጠው ልዩ ሀይል መሆኑን በማብራራት ይህ ዕዝ አስካሁን ለሀገር ለከፈለው ዋጋ ኢትዮጵያ እንደምታከብረውና ነገም ይህንኑ ልዩ ብቃቱን ይዞ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል፡፡ ሠራዊቱ መስዋዕትነት የከፈለውና እየከፈለ የሚገኘው ሀገርን ለማሻገር መሆኑን ገልጸው፣ ይህም ሠራዊቱን ሀገርን ከውጭ ጠላት ከመከላከል ባለፈ፣ የውስጥ ሰላምን በማጽናት ህልውናችን ተጠብቆ ዕድገት እንዲቀጥል የሚያስችል የዜጎች ክብር መገለጫ አድርጎታል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው ሻዕቢያ ከጅምሩ ኢትዮጵያን ከባሕር በር ለማራቅ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር ፅምዶ ፈጥሮ ኢትዮጵያ ላይ ደባ የሰራ ሃይል መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ ሕገ-ወጡ ህወሓትም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ የሸጠና ለ27 ዓመታት ስልጣን ይዞ ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ አጠንክሮ የሰራ ቅጥረኛ የገዛ ሀገሩን ሠራዊት ያጠቃ የክህደት ሃይል ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በሕወሃት ክህደት የተፈተነች ነገር ግን ፀንታ የቆመች የልዩ ዘመቻ ሠራዊት መሰል ጠንካራ አርበኛ ልጆች ያሏት ሀገር ስለሆነች ጉዞዋን ቀጥላለች ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። ፅንፈኞቹን የጥፋት ሃይሎች በባዕዳን ስትራቴጂ ሥር ተሰልፈው ኢትዮጵያን የማዳከምና የማፍረስ ፅምዶ የተባለ ጥምረት ቀርፀው ሕዝባችንን ለስቃይና መከራ በመዳረግ ደካማ ኢትዮጵያን ለማየት ጓጉተው ቢሠሩም ይህ ፍላጎታቸው መቼም ሊሳካ አይችልም ብለዋል። ህወሃት የኢትዮጵያን ሕዝብ በመከፋፈል እርስ በርሱ እንዳይተማመን ሲሰራ የኖረ እኩይ ፖለቲካ አራማጅ ፀረ-ሀገር ሃይል ነው ብለዋል። ዛሬ ሴራው ከሽፎ የትግራይ ህዝብን ጨምሮ አጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ የዚህን መሰሪ ቡድን መጥፎ ተግባር ተርድቷል ብለዋል። አሁን ላይ ህወሃት ለሻዕቢያ እየተላላከና የቀድሞ ጠላቶቹን ጽንፈኛ ሸኔንና ፅንፈኛ ፋኖን አቅፎ የትላንት ክህደቱን በአደባባይ እየደገመው ይገኛልም ብለዋል። ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ በጀመረችው እድገትና ብልፅግና ወደፊት ትቀጥላለች፤ የታሪካዊ ጠላቶቿ ህልም አይሳካም ሲሉም ገልጸዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በአሁኑ ወቅት በትጥቅም በሰው ሀይል ግንባታ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በማስታወስ ለሰፈር ባንዳዎች ብቻ ሳይሆን በየትኛውም አቅጣጫ በሀገር ላይ ለሚቃጣ ጥቃት ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በአስተማማኝ ዝግጁነት ላይ መሆኑን ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚወስዱበት ነው
Aug 14, 2026 276
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚወስዱበት መሆኑን በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ሕብረት የሳህራዊ ሪፐብሊክ አምባሳደር ላሚን ባአሊ ገለጹ። አምባሳደር ባአሊ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በሌሎች ዘርፎች ስኬታማ ጉዞ እያደረገች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ስኬታማ ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንም አንስተዋል። ይህ ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ዜጎች የፖለቲካ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ አዎንታዊ ማረጋገጫ እንደሆነም ነው የተናገሩት። በምርጫው የፖለቲካ ፓርቲዎች በንቃት መሳተፋቸውን በመጥቀስ፣ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ውስጥ በጎ እርምጃ መሆኑንም አምባሳደር ባአሊ አስረድተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው የሪፎርም አጀንዳ በሀገሪቱ ውስጥ ለበለጠ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ልማት ዕድገት አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በተጣጣመ መልኩ የሚከናወኑ የተለያዩ የልማትና የለውጥ ሥራዎች አዎንታዊ ውጤት እያመጡ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። በሀገሪቱ እየተተገበረ ያለው የኢኮኖሚ ሪፎርም የዜጎችን ኑሮ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ጨምረው አንስተዋል፡፡ ይህ በኢትዮጵያ እውን እየሆነ ያለው ውጤታማ ሪፎርም በዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትና እውቅና ማግኘቱን ተናግረዋል። በመሆኑም ይህ የኢትዮጵያ ስኬታማ ተሞክሮ በአጠቃላይ በአፍሪካ ደረጃ የሚገኙ ሌሎች ሀገራት ትምህርት ሊወስዱበት የሚችል ነው ብለዋል። ሀገራዊ ምክክር አስፈላጊ የፖለቲካ ልምምድ እንደሆነ የጠቆሙት አምባሳደሩ፣ በኢትዮጵያ እየተደረገ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ለሁሉም አካላት ዘላቂ ጥቅም ለማስገኘት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል። በሳህራዊ ሪፐብሊክ እና በኢትዮጵያ መካከል እ.ኤ.አ ከ1970ዎቹ ጀምሮ የነበረውን ትብብር አውስተው፣ የሀገራቱ ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰዋል። ባህል፣ ስፖርት፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ጤና እና ሌሎች የጋራ ፍላጎት በሆኑ ዘርፎች የሁለትዮሽ ትብብሩን የበለጠ ለማስፋት እንደሚሰራም አምባሳደር ላሚን ባአሊ ገልጸዋል።
የምክክር ጉባኤው የመመካከር ባህልን በማዳበር ሀገራዊ መግባባትን እያጠናከረ ነው
Aug 14, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በኢትዮጵያ የመመካከር ባህልን በማዳበር ሀገራዊ መግባባትን የሚያጠናክር መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ናቸው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ በህዝቦች መካከል የማይናወጥ ወዳጅነትን ለመገንባት እና በጽኑ መሠረት ላይ የተገነባች ሀገርን ለማስቀጠል ከፍተኛ ተስፋ የተጣለበት ታሪካዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ እሸቱ ኤራቦ እንዳሉት፤ የምከክር ጉባኤው ለዘመናት ማህበረሰቡ ሲያነሳቸው ለነበሩ ጥያቄዎች መፍትሄ ለመስጠት ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ ማማ ለማድረስ የሚያሰችል ነው። ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች፣ የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለማስረከብ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።   አቶ ባንቲሁን ትዛዙ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ ባህላዊ የእርቅና የመመካከር እሴት እንዲያንሰራራ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። ምክክሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ማዕዘናት የመጡ ማህበረሰቦችን በአንድ ጥላ ስር በማገናኘት የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ትስስር ለማጠናከር ማስቻሉን አብራርተዋል። ሀሳቦችን በነጻነት ወደ መድረክ ማምጣትና በግልጽነት መነጋገር ለዘላቂ ሰላምና ግንባታ ትልቅ መሰረት መሆኑን የገለጹት ደግሞ አቶ ዘሪሁን ገብረእግዚአብሔር ናቸው።   ተመካካሪዎቹ በሰፊ የቡድን ውይይቶች ያነሷቸው ነጥቦች ሀገራዊ አጀንዳዎችን በስፋትና በጥልቀት ያቀፉ በመሆናቸው፣ ሂደቱ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።  
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ ነው
Aug 14, 2026 176
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት አቀራረብ ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ መሆኑን የኢትዮጵያ የሕዝብ ዲፕሎማሲ ኢንስቲትዩት ፕሬዚዳንት ያሲን አሕመድ ገለጹ። የኢንስቲትዩቱ ፕሬዚዳንት ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በፖለቲካ መሪዎችና በመንግሥት መካከል ከሚደረጉ ምክክሮች በተለየ ወደ ሕዝብ በመውረድ ከታች ወደ ላይ የመጣ ሂደት ነው። በአፍሪካ በርካታ ሀገራት የሚካሄዱ ሀገራዊ ምክክሮች የሕዝብን ስጋትና ምኞት በማያንጸባርቅ መልኩ በመሪዎች ደረጃ በሚደረሱ ስምምነቶች ተጀምሮ ለሕዝብ የሚቀርቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የምክክር ጉባኤ ግን ከታችኛው የማኅበረሰብ ክፍል ጀምሮ የሕዝብ ተሳትፎንና አካታችነትን በማረጋገጥ ወደ ብሔራዊ ደረጃ የሚሸጋገር ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በምክክር ጉባኤው የታደሙ የተለያዩ የማኅበረሰብ ተወካዮች ስብጥርና ተሳትፎም የምክክሩን አሳታፊና አካታችነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤውም የዜጎችን ስጋቶችና ቅድሚያ የሚሰጧቸውን ዐበይት አጀንዳዎች በመለየት ወደ ብሔራዊ አጀንዳ ለማምጣት ያለመ ወሳኝ መድረክ መሆኑን አብራርተዋል። ይህም በዘመናዊት ኢትዮጵያ የሀገር ግንባታ ሂደትና ታሪክ ውስጥ ሁሉንም ዜጎች ማዕከል በማድረግ በተቋማዊና ፖለቲካዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መቀራረብን የሚገነባ አቀራረብ መሆኑን አስረድተዋል። የምክክር ጉባኤው ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ያላትን ሕብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን የዘመናት ውስብስብ ጉዳዮች በሰለጠነ የምክክር መድረክ ለመመልከትና የጋራ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያግዝ ጠቁመዋል። በሰለጠነ ዓለም ውስጥ የትጥቅ ትግል ቁርሾንና መቃቃርን የሚያባብስ እንጂ ሰላምን የሚያመጣ አይደለም ያሉት ያሲን አሕመድ፤ በመርህ ላይ የተመሠረተ ምክክር ለዘላቂ ሀገር ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአመፅና አዋኪ የትጥቅ ትግል ሀገርን በማጎሳቆል የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት፣ የዕድገትና የልማት ፍላጎት ከማቀጨጭ ያለፈ አንዳች ፋይዳ እንደሌለው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ አካታችና አሳታፊ የምክክር ጉባኤም የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማጎልበት በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመገንባት እንደሚረዳ አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ በፓርላማ በጸደቀ ሕግ መሠረት የተቋቋመና በነጻ ኮሚሽን የሚመራ መሆኑም ለምክክር ጉባኤው ሂደት ተቋማዊና ሕጋዊ መሠረት መስጠቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ከታች ጀምሮ የመጣበት አቀራረብም ልዩነቶችን ለማስተዳደር፣ መግባባትን ለመገንባትና ዘላቂ የፖለቲካ መፍትሔ ለማስገኘት ጠቃሚ ተሞክሮ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት አቀራረብ ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ መሆኑን አስረድተዋል።
የፀረ ሙስና ትግሉ የህዝብና የመንግሥት ቋሚ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት - ምክትል አፈ ጉባዔ ሎሚ በዶ
Aug 14, 2026 195
አዳማ፤ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና ትግል የሕዝብና የመንግሥት ዘላቂና ዋና አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ። የፌዴራል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓል ማጠቃለያ መድረክ "የፀረ ሙስና ትግል ትናንት ዛሬ እና ነገ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዳማ አየተካሄደ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፤ ዛሬ የምናከብረው የጸረ ሙስና ትግል ያለፈውን ለመዘከር ብቻ ሳይሆን፣ ያለንበትን ለመገምገምና ወደፊት የምንመራበትን አቅጣጫ ለመወሰን የሚያስችለን ነው ብለዋል። በሀገራዊ ምክክሩ ዋና ዋና መወያያ ነጥቦች መካከል ሙስና እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች በግንባር ቀደምትነት የተቀመጠ አጀንዳ መሆኑን አንስተው፤ የፀረ-ሙስና ትግሉ የአንድ ተቋም ብቻ ሳይሆን የመላው ህዝብ የጋራ ሀገራዊ ህልውና ጉዳይ መሆኑን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። ባለፉት 25 ዓመታት ኮሚሽኑ በሶስት ዋና ዋና የትግል አዕማድ ላይ ተመስርቶ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን ያስታወሱት ምክትል አፈ ጉባኤዋ፤ የዜጎችን አስተሳሰብ የሚቀርፅ የሥነምግባር ግንባታ፣ የሌብነት ቀዳዳዎችን የሚደፍን የሙስና ቅድመ-መከላከል እና ጥፋተኞችን ለፍትህ የሚያቀርብ የህግ ማስከበር ስራዎች ናቸው ብለዋል። እነዚህ ሶስት መሰረቶች የፀረ-ሙስና ትግሉ የማዕዘን ድንጋዮች ሆነው አሁንም ያገለግላሉ ሲሉ አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ በ25 ዓመታት የሥራ ጉዞው በሥነ-ምግባር ግንባታ፣ በሙስና መከላከል፣ የሕዝብ ግንዛቤን በማሳደግ፣ በተቋማት የፀረ-ሙስና አቅም ማጠናከርና በተጠያቂነት ስርዓት ዝርጋታ ከሁሉ በላይ ሙስናን የሚጠየፍ ማህበረሰብ ከመፍጠር አንፃር በርካታ ሥራዎችን አከናውኗል ነው ያሉት።   በአሁኑ ወቅት መንግስት ሙስናን ለመታገል ዘመናዊ እና መዋቅራዊ የሪፎርም ስራዎችን በስፋት እየተገበረ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በተለይም ሀገራዊ የጥቆማ መቀበያ ስርዓት፣ የዜጎችን ድምፅ ያለስጋት እንዲሰማ አድርጓል ብለዋል። ዲጂታል የሀብት ማሳወቂያ እና ማስመዘገቢያ ስርዓት ደግሞ የመንግስት ተቋማት አመራር እና ሰራተኞች ሀብት ለህዝብ ግልጽ ማድረጉን ያነሱት አፈ ጉባዔዋ፤ በመሶብ የአንድ መስኮት አገልግሎትና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የተደገፉ አሰራሮች ሌብነትን በቴክኖሎጂ አቅም የሚያጋልጡ አዲስ የትግል ምዕራፎች መሆናቸውን አውሰተዋል። ሙስና የገንዘብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሥነ-ምግባር፣ የሞራል፣ የአስተዳደር፣ የፍትሕ፣ የልማት፣ የሀገር እና የትውልድ ግንባታ ጉዳይ በመሆኑ ሁሌም ቋሚ የህዝብና የመንግሥት አጀንዳ ሆኖ ሊቀጥል እንደሚገባም ወይዘሮ ሎሚ አስገንዝበዋል።    

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ለማንኛውም ጥቃት ፈጣን ምላሽ ሰጪና ስጋቶችን አስቀድሞ መከላከል የሚችል የመላ ሠራዊቱ ሞዴል ኃይል ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Aug 14, 2026 137
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ) ፦ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በተለየ ወታደራዊ ጥበብ በፍጥነት ፈጣን ምላሽ ሰጪና አስቀድሞ ስጋቶችን መከላከል የሚችል የመከላከያ ዋነኛ ስትራቴጂካዊ መቺ ሀይል ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ፡፡ ኢታማዦር ሹሙ በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ውይይት ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ስለወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ለሠራዊቱ አመራሮች የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሥርዓት ለውጥ አድርጋ ገና ሳትረጋጋ ባንዳዎች ባደረሱባት ጥቃት ሀገር በተፈተነችበት ወቅት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ሠራዊት የተደቀነውን አደጋ በመቀልበስ ረገድ ከባድ የተጋድሎ አድርጓል ሲሉም በበመድረኩ ላይ ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት የውጊያ ማርሽ ቀያሪ የምድር ድሮን የሚል ስያሜ የተሰጠው ልዩ ሀይል መሆኑን በማብራራት ይህ ዕዝ አስካሁን ለሀገር ለከፈለው ዋጋ ኢትዮጵያ እንደምታከብረውና ነገም ይህንኑ ልዩ ብቃቱን ይዞ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል፡፡ ሠራዊቱ መስዋዕትነት የከፈለውና እየከፈለ የሚገኘው ሀገርን ለማሻገር መሆኑን ገልጸው፣ ይህም ሠራዊቱን ሀገርን ከውጭ ጠላት ከመከላከል ባለፈ፣ የውስጥ ሰላምን በማጽናት ህልውናችን ተጠብቆ ዕድገት እንዲቀጥል የሚያስችል የዜጎች ክብር መገለጫ አድርጎታል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው ሻዕቢያ ከጅምሩ ኢትዮጵያን ከባሕር በር ለማራቅ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር ፅምዶ ፈጥሮ ኢትዮጵያ ላይ ደባ የሰራ ሃይል መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ ሕገ-ወጡ ህወሓትም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ የሸጠና ለ27 ዓመታት ስልጣን ይዞ ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ አጠንክሮ የሰራ ቅጥረኛ የገዛ ሀገሩን ሠራዊት ያጠቃ የክህደት ሃይል ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በሕወሃት ክህደት የተፈተነች ነገር ግን ፀንታ የቆመች የልዩ ዘመቻ ሠራዊት መሰል ጠንካራ አርበኛ ልጆች ያሏት ሀገር ስለሆነች ጉዞዋን ቀጥላለች ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። ፅንፈኞቹን የጥፋት ሃይሎች በባዕዳን ስትራቴጂ ሥር ተሰልፈው ኢትዮጵያን የማዳከምና የማፍረስ ፅምዶ የተባለ ጥምረት ቀርፀው ሕዝባችንን ለስቃይና መከራ በመዳረግ ደካማ ኢትዮጵያን ለማየት ጓጉተው ቢሠሩም ይህ ፍላጎታቸው መቼም ሊሳካ አይችልም ብለዋል። ህወሃት የኢትዮጵያን ሕዝብ በመከፋፈል እርስ በርሱ እንዳይተማመን ሲሰራ የኖረ እኩይ ፖለቲካ አራማጅ ፀረ-ሀገር ሃይል ነው ብለዋል። ዛሬ ሴራው ከሽፎ የትግራይ ህዝብን ጨምሮ አጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ የዚህን መሰሪ ቡድን መጥፎ ተግባር ተርድቷል ብለዋል። አሁን ላይ ህወሃት ለሻዕቢያ እየተላላከና የቀድሞ ጠላቶቹን ጽንፈኛ ሸኔንና ፅንፈኛ ፋኖን አቅፎ የትላንት ክህደቱን በአደባባይ እየደገመው ይገኛልም ብለዋል። ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ በጀመረችው እድገትና ብልፅግና ወደፊት ትቀጥላለች፤ የታሪካዊ ጠላቶቿ ህልም አይሳካም ሲሉም ገልጸዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በአሁኑ ወቅት በትጥቅም በሰው ሀይል ግንባታ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በማስታወስ ለሰፈር ባንዳዎች ብቻ ሳይሆን በየትኛውም አቅጣጫ በሀገር ላይ ለሚቃጣ ጥቃት ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በአስተማማኝ ዝግጁነት ላይ መሆኑን ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የምክክር ጉባኤው የመመካከር ባህልን በማዳበር ሀገራዊ መግባባትን እያጠናከረ ነው
Aug 14, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በኢትዮጵያ የመመካከር ባህልን በማዳበር ሀገራዊ መግባባትን የሚያጠናክር መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ናቸው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ በህዝቦች መካከል የማይናወጥ ወዳጅነትን ለመገንባት እና በጽኑ መሠረት ላይ የተገነባች ሀገርን ለማስቀጠል ከፍተኛ ተስፋ የተጣለበት ታሪካዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ እሸቱ ኤራቦ እንዳሉት፤ የምከክር ጉባኤው ለዘመናት ማህበረሰቡ ሲያነሳቸው ለነበሩ ጥያቄዎች መፍትሄ ለመስጠት ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ ማማ ለማድረስ የሚያሰችል ነው። ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች፣ የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለማስረከብ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።   አቶ ባንቲሁን ትዛዙ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ ባህላዊ የእርቅና የመመካከር እሴት እንዲያንሰራራ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። ምክክሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ማዕዘናት የመጡ ማህበረሰቦችን በአንድ ጥላ ስር በማገናኘት የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ትስስር ለማጠናከር ማስቻሉን አብራርተዋል። ሀሳቦችን በነጻነት ወደ መድረክ ማምጣትና በግልጽነት መነጋገር ለዘላቂ ሰላምና ግንባታ ትልቅ መሰረት መሆኑን የገለጹት ደግሞ አቶ ዘሪሁን ገብረእግዚአብሔር ናቸው።   ተመካካሪዎቹ በሰፊ የቡድን ውይይቶች ያነሷቸው ነጥቦች ሀገራዊ አጀንዳዎችን በስፋትና በጥልቀት ያቀፉ በመሆናቸው፣ ሂደቱ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።  
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ ነው
Aug 14, 2026 176
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት አቀራረብ ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ መሆኑን የኢትዮጵያ የሕዝብ ዲፕሎማሲ ኢንስቲትዩት ፕሬዚዳንት ያሲን አሕመድ ገለጹ። የኢንስቲትዩቱ ፕሬዚዳንት ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በፖለቲካ መሪዎችና በመንግሥት መካከል ከሚደረጉ ምክክሮች በተለየ ወደ ሕዝብ በመውረድ ከታች ወደ ላይ የመጣ ሂደት ነው። በአፍሪካ በርካታ ሀገራት የሚካሄዱ ሀገራዊ ምክክሮች የሕዝብን ስጋትና ምኞት በማያንጸባርቅ መልኩ በመሪዎች ደረጃ በሚደረሱ ስምምነቶች ተጀምሮ ለሕዝብ የሚቀርቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የምክክር ጉባኤ ግን ከታችኛው የማኅበረሰብ ክፍል ጀምሮ የሕዝብ ተሳትፎንና አካታችነትን በማረጋገጥ ወደ ብሔራዊ ደረጃ የሚሸጋገር ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በምክክር ጉባኤው የታደሙ የተለያዩ የማኅበረሰብ ተወካዮች ስብጥርና ተሳትፎም የምክክሩን አሳታፊና አካታችነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤውም የዜጎችን ስጋቶችና ቅድሚያ የሚሰጧቸውን ዐበይት አጀንዳዎች በመለየት ወደ ብሔራዊ አጀንዳ ለማምጣት ያለመ ወሳኝ መድረክ መሆኑን አብራርተዋል። ይህም በዘመናዊት ኢትዮጵያ የሀገር ግንባታ ሂደትና ታሪክ ውስጥ ሁሉንም ዜጎች ማዕከል በማድረግ በተቋማዊና ፖለቲካዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መቀራረብን የሚገነባ አቀራረብ መሆኑን አስረድተዋል። የምክክር ጉባኤው ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ያላትን ሕብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን የዘመናት ውስብስብ ጉዳዮች በሰለጠነ የምክክር መድረክ ለመመልከትና የጋራ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያግዝ ጠቁመዋል። በሰለጠነ ዓለም ውስጥ የትጥቅ ትግል ቁርሾንና መቃቃርን የሚያባብስ እንጂ ሰላምን የሚያመጣ አይደለም ያሉት ያሲን አሕመድ፤ በመርህ ላይ የተመሠረተ ምክክር ለዘላቂ ሀገር ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአመፅና አዋኪ የትጥቅ ትግል ሀገርን በማጎሳቆል የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት፣ የዕድገትና የልማት ፍላጎት ከማቀጨጭ ያለፈ አንዳች ፋይዳ እንደሌለው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ አካታችና አሳታፊ የምክክር ጉባኤም የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማጎልበት በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመገንባት እንደሚረዳ አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ በፓርላማ በጸደቀ ሕግ መሠረት የተቋቋመና በነጻ ኮሚሽን የሚመራ መሆኑም ለምክክር ጉባኤው ሂደት ተቋማዊና ሕጋዊ መሠረት መስጠቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ከታች ጀምሮ የመጣበት አቀራረብም ልዩነቶችን ለማስተዳደር፣ መግባባትን ለመገንባትና ዘላቂ የፖለቲካ መፍትሔ ለማስገኘት ጠቃሚ ተሞክሮ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት አቀራረብ ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ መሆኑን አስረድተዋል።
የግብፅ ሚዲያዎች ስለ ህዳሴ ግድብ ከራሳቸው ባለሙያዎች ሳይንሳዊ ግኝቶች ጋር የሚቃረን ዘገባ እያቀረቡ ነው-ጋዜጠኛና ፀሐፊ ዛሂድ ዚዳን
Aug 14, 2026 224
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ):- የግብፅ ሚዲያዎች ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሚያቀርቧቸው ዘገባዎች ወጥነት የሌላቸው እና ከበርካታ የግብፅ ሳይንቲስቶችና የውሃ ባለሙያዎች ሳይንሳዊ ግምገማዎች ጋር የሚጋጩ መሆናቸውን ጋዜጠኛና ፀሐፊ ዛሂድ ዚዳን ገለጹ። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡት ዛሂድ፤ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ የሚደረጉ ክርክሮች በሳይንሳዊና ቴክኒካዊ ትንተናዎች ላይ ከማተኮር ይልቅ አሻሚና እርስ በእርስ በሚቃረኑ የመገናኛ ብዙሃን ተረኮች የሚመሩ መሆናቸውን ተናግሯል። የግብፅ የጂኦሎጂ ባለሙያ ዶክተር አባስ ሸራቂ ግድቡ በተፈጥሮው በግብፅ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደማያደርስ በግልጽ ካስረዱት የሀገሪቱ ባለሙያዎች መካከል አንዱ እንደሆኑ ጋዜጠኛው ጠቅሰዋል። ሌላኛው የግብፅ ሳይንቲስት ዶክተር ሳመህ አርማኒዮስ፤ ህዳሴ ግድብ በወንዙ ፍሰት ላይ ምንም ዓይነት የውሃ እጥረት ሳይፈጥር ኤሌክትሪክ አመንጭቶ ውሃው በቀጥታ ወደ ወንዙ የሚመለስበት የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት መሆኑን ማብራራታቸውን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የህዋ ሳይንቲስቱ ዶክተር ፋሩክ ኤል-ባዝ ግድቡ የተሻለ የውሃ አስተዳደር እንዲኖር በማድረግ የኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የሱዳንን እና የግብፅንም ጥቅም ለማስጠበቅ እንደሚረዳ ማመልከታቸውን ዛሂድ አብራርተዋል።   ጋዜጠኛው እንደ ፕሮፌሰር ሰይፍ አል-ዲን ሀማድ እና የቀድሞ የሱዳን የውሃና መስኖ ሚኒስትር ኡስማን አል-ቶም ያሉ የሱዳን ባለሙያዎችን በመጥቀስ፤ ስለ አባይ ወንዝ በሚደረጉ ውይይቶች ላይ በፖለቲካዊ ጩኸት ሳይሆን በሳይንሳዊና በተረጋገጡ ማስረጃዎች ላይ የተመሰረተ ትንተና ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ማሳሰባቸውን ገልጸዋል። አንዳንድ የግብፅ መገናኛ ብዙሃን ግድቡን በአንድ ወቅት ከጎርፍና የመሠረተ ልማት ውድመት ጋር በማያያዝ፣በሌላ ጊዜ ደግሞ የውሃ መጠን መቀነስና ድርቅ ያስከትላል በማለት የሚከሱበት መንገድ ፍጹም የሚቃረን ሀሳብ ነው ብለዋል። ዛሂድ አክለው እንደገለጹት፤ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ አደጋ ይደቅናል የሚሉ የፖለቲከኞችና የመገናኛ ብዙሃን ውንጀላዎች ፖለቲካዊ ፍላጎትን ያዘሉ እንጂ ወጥ የሆነ ሳይንሳዊ መሰረት የሌላቸው ናቸው። ይህ አይነቱ የተሳሳተ ትርክት ኢትዮጵያ ወደ ተፋሰሱ ሀገራት ከሚፈሰው የናይል ውሃ 86 በመቶ ድርሻ ካለው ከአባይ ወንዝ የተፈጥሮ ሀብቷ የመልማት መብቷን ለማደናቀፍ ለበርካታ አስርታት ሲከናወን የቆየ አካሄድ እንደሆነም ነው ያስረዱት።   አጠቃላይ የአባይ ወንዝ ዓመታዊ የውሃ መጠን በክረምቱ ወራት ወዲያው ሊታወቅ የሚችል ባለመሆኑ፣ ስለ ውሃው መጠን ቀድሞ ድምዳሜ መስጠት አይቻልም ነው ያሉት ዛሂድ። ይልቁንም የግብጽ መገናኛ ብዙሃን ከፖለቲካዊ ጩኸት በመውጣት በሳይንሳዊ ጥናቶችና በተረጋገጡ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ሚዛናዊ ዘገባ እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ በሀገራችን ጉዳይ እኩል የመሳተፍና የመወሰን ዕድልን አረጋግጦልናል
Aug 14, 2026 277
ጂንካ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ እኔ አውቅልሃለው የሚለውን አግላይ አካሄድ በማስቀረት ዜጎች በሀገር ጉዳይ እኩል የመሳተፍና የመወሰን መብታቸውን ያረጋገጠ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የበና ፀማይ ወረዳ አርብቶ አደሮች ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ የዘመናት ችግሮችን መፍትሄ በመስጠት ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምና ልማትን በማስፈን ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ጉልህ ሚና እንዳለው የታመነበት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወደማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ሀገራዊ ምክክሩን አስመልክቶ ኢዜአ በበናፀማይ ወረዳ ያነጋገራቸው አርብቶ አደሮች እንዳሉት፤ ምክክሩ ለሁሉም ዜጎች በሀገር ጉዳይ ላይ እኩል የመሳተፍና የመወሰን እድልን ከመስጠት ባለፈ የቆዩ አለመግባባቶችን በምክክር ለመፍታት ያስችላል። ከአርብቶ አደሮቹ መካከል የበናፀማይ ወረዳ የሀገር ሽማግሌ አቶ ጀሞ ቦሎቾ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ከዚህ ቀደም የመደመጥ ዕድል ላላገኘው የአካባቢው አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ጭምር የመደመጥና በሀገሩ ጉዳይ ከሌሎች እኩል ውሳኔ የመስጠት መብቱን እንዳረጋገጠለት ተናግረዋል። ቀደም ሲል የአርብቶ አደሩ አካባቢ የግጭት ቀጠና እና የሰላም እጦት በስፋት የሚስተዋልበት እንደነበረ አስታውሰው፥ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የተለዩ አጀንዳዎች መሰል ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊያን በጋራ ቁጭ ብለው መምከራቸው ለቆዩ ችግሮችና አለመግባባቶች መፍትሄ ለማምጣት ያስችላቸዋል ያሉት የሀገር ሽማግሌው፣ የምክክሩ ውጤትም ለአካባቢያቸውም ተጨባጭ ውጤት ያመጣል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል። ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርብቶ አደር ጋርሾ ማያ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ተሳታፊዎች አካታች በሆነ መንገድ የተመረጡ እና የእነሱም ወኪሎች የተገኙበት መሆኑንን ገልጸዋል።   ይህም ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች በምክክሩ እንዲደመጡና በሀገር ጉዳይ የመወሰን መብት እንዲኖራቸው ያደርጋል ብለዋል። እንደ አርብቶ አደር ጋርሾ ገለጻ፣ የምክክር ሂደቱ ሁሉንም ማህበረሰብ በየደረጃው ያሳተፈ እና የሁሉም ሀሳብ የተካተተበት ስለሆነ ለሀገር ዘላቂ ሰላምና እድገት መረጋገት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ በሀገራዊ ምክክር ኮሚሸን ተለይተው ውይይት እየተደረገባቸው ያሉ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችም በየአካባቢው የሚነሱ ፍላጎቶችን ያማከሉ እንደሆነ ጠቅሰው፣ በአጀንዳዎች ላይ የሚደረስበት መግባባትም ሀገራዊ አንድነትን ከማጠናከር ባለፈ ለሁሉም ምቹ የሆነች ሀገር ለመገንባት ያስችላል ብለዋል። ምክክሩ ሀገርን ተብትበው ከያዙ ችግሮች በማላቀቅ ወደከፍታ ማማ የሚያወጣት ታሪካዊ ዕድል ነው ያሉት ደግሞ የወረዳው ነዋሪ አርብቶ አደር አርቲ ማያ ናቸው።   የግጭትና ያለመግባባት መንስኤዎች ተቀራርቦ የመነጋገር ዕድልን ማጣት መሆኑን ጠቁመው፣ ምክክሩ ችግሮችን ለመፍታት ብቻ ሳይሆን የመመካከር ባህልን በማሳደግ ለዘላቂ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ይህን ታሪካዊ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ለሁሉም ምቹ የሆነች ሀገር መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል። የምክክር ጉባኤው ብዙ ውጣውረዶችን አልፎ መጨረሻው ምዕራፍ ላይ በመድረሱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው፣ ምክክሩ ሁሉን በእኩል አሳታፊ መሆኑ እኔ አውቅልሃለው የሚለውን አግላይ አካሄድ አስቀርቷል ብለዋል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ባለው ዋናው የምክክር ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን የወከሉ 4 ሺህ ተመካካሪዎች በተለዩ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው
Aug 14, 2026 219
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ) ፦ የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ የተቋማት አፈፃፀምን ጨምሮ፣ የሴፍቲኔት፣ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተከናወኑ ተግባራትና ሌሎች ኢኒሼቲቮችን ገምግሟል።   የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው። ዛሬ ለአንድ ሰው የዘራነው ተስፋ ነገ ለማኅበረሰባችን የሚያፈራ ፍሬ ይሆናል፣ ዛሬ የረዳነው ወገን ነገ ሌላውን ለመርዳት የሚነሳ ዜጋ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። በጎ ፈቃድ አንድ ጊዜ የሚደረግ ተግባር ሳይሆን ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር የመልካምነት ባህል በመሆኑ ባህሉን በማዳበር ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል። በሌላ በኩል በክልሉ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የቅዳሜ ገበያዎችን ተደራሽ በማድረግ የተጀመሩ ተግባራትን ማጎልበት እንደሚገባ ገልፀዋል። ዜጎችን ከተረጂነትና ከጥገኝነት በማላቀቅ ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙ ምርታማነታቸውን በማሳደግ የተጀመሩ ተግባራትም ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ሁሉም አመራር የበኩሉን ሀላፊነት እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ የመንግስት እና የፓርቲ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በምክክር ጉባኤው እየተነሱ ያሉት ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው
Aug 14, 2026 208
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከተመካካሪዎች እየተነሱ የሚገኙ ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገትና የተሻለ መጻኢ ጊዜ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ተመካካሪ አበራ አኔቦ፤ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደፊት የሚያሻግሩና የጋራ ሀገርን መገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች ከተመካካሪዎች እየተነሱ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው ምክክር ለሀገራችን ዘላቂ ጥቅም የሚያስገኝ እና ለመጪው ትውልድም መልካም አርአያ የሚሆን ታሪካዊ ጉባኤ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ይህም ለኢትዮጵያ ቀጣይነት ላለው ዘላቂ ዕድገት ምቹ ዕድል ይዞ እንደሚመጣ ታላቅ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። ተመካካሪ ወይዘሮ ኦድንጊሊ ሎ፤ አካታች እና አሳታፊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እጅግ አስፈላጊ በሆነ ወቅት መከናወኑን ሂደቱም የተሳካና የኢትዮጵያን የወደፊት ጉዞ የሚያስቀጥሉ መልካም አጋጣሚዎችን መፍጠሩን ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያንን በተወካዮቻቸው በምልዓተ ያሳተፈ መሆኑንና ኢትዮጵያን አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስችሉ ጠቃሚ ሀሳቦች በነጻነት እንዲነሱ ምቹ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሀገሪቱን ብዝሃነት ያንጸባረቀ እና ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ አዎንታዊ የምክክር ጉባኤ እንደሆነም ነው ያነሱት። ሌላኛው ተመካካሪ ​ታደሰ ዳኜ በበኩላቸው፤ ለሀገር አንድነት ምክክር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝና መልካም ውጤት ይዞ ይመጣል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል። ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች የወከሉ ተመካካሪዎች በነጻነትና አሳታፊ በሆነ መልኩ እየተመካከሩ በመሆኑ ሀገራዊ ምክክሩ ውጤታማ ነው ብለዋል።
የምክክር ጉባኤው የዘመናት ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት ነው-ተመካካሪዎች 
Aug 14, 2026 213
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታትና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ የጋራ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በምክክሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች፤ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የጋራ የመፍትሔ ሀሳብ የቀረበበት መሆኑን ተናግረዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ነኢ አለልኝ ምክክሩ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግር ጠቃሚ ግብአቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በሀገሪቱ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮች ላይ በስፋት ተመካክረን የመፍትሔ ሀሳቦችን አስቀምጠናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ኒሽራ ሱሌይማን ሀሳባችንን በነጻነትና በግልጽ በማቅረብ የመፍትሄ ሀሳቦች ላይ ምክክር እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። ምክክሩ መግባባት የሰፈነባት ያደገችና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ምክክሩ ለሀገር የሚበጁ ጠቃሚ ግብዓቶች የተገኙበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ደራራ ጣፋ ናቸው።
ፖለቲካ
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ለማንኛውም ጥቃት ፈጣን ምላሽ ሰጪና ስጋቶችን አስቀድሞ መከላከል የሚችል የመላ ሠራዊቱ ሞዴል ኃይል ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Aug 14, 2026 137
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ) ፦ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በተለየ ወታደራዊ ጥበብ በፍጥነት ፈጣን ምላሽ ሰጪና አስቀድሞ ስጋቶችን መከላከል የሚችል የመከላከያ ዋነኛ ስትራቴጂካዊ መቺ ሀይል ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ፡፡ ኢታማዦር ሹሙ በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ውይይት ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ስለወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ለሠራዊቱ አመራሮች የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሥርዓት ለውጥ አድርጋ ገና ሳትረጋጋ ባንዳዎች ባደረሱባት ጥቃት ሀገር በተፈተነችበት ወቅት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ሠራዊት የተደቀነውን አደጋ በመቀልበስ ረገድ ከባድ የተጋድሎ አድርጓል ሲሉም በበመድረኩ ላይ ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት የውጊያ ማርሽ ቀያሪ የምድር ድሮን የሚል ስያሜ የተሰጠው ልዩ ሀይል መሆኑን በማብራራት ይህ ዕዝ አስካሁን ለሀገር ለከፈለው ዋጋ ኢትዮጵያ እንደምታከብረውና ነገም ይህንኑ ልዩ ብቃቱን ይዞ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል፡፡ ሠራዊቱ መስዋዕትነት የከፈለውና እየከፈለ የሚገኘው ሀገርን ለማሻገር መሆኑን ገልጸው፣ ይህም ሠራዊቱን ሀገርን ከውጭ ጠላት ከመከላከል ባለፈ፣ የውስጥ ሰላምን በማጽናት ህልውናችን ተጠብቆ ዕድገት እንዲቀጥል የሚያስችል የዜጎች ክብር መገለጫ አድርጎታል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው ሻዕቢያ ከጅምሩ ኢትዮጵያን ከባሕር በር ለማራቅ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር ፅምዶ ፈጥሮ ኢትዮጵያ ላይ ደባ የሰራ ሃይል መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ ሕገ-ወጡ ህወሓትም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ የሸጠና ለ27 ዓመታት ስልጣን ይዞ ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ አጠንክሮ የሰራ ቅጥረኛ የገዛ ሀገሩን ሠራዊት ያጠቃ የክህደት ሃይል ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በሕወሃት ክህደት የተፈተነች ነገር ግን ፀንታ የቆመች የልዩ ዘመቻ ሠራዊት መሰል ጠንካራ አርበኛ ልጆች ያሏት ሀገር ስለሆነች ጉዞዋን ቀጥላለች ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። ፅንፈኞቹን የጥፋት ሃይሎች በባዕዳን ስትራቴጂ ሥር ተሰልፈው ኢትዮጵያን የማዳከምና የማፍረስ ፅምዶ የተባለ ጥምረት ቀርፀው ሕዝባችንን ለስቃይና መከራ በመዳረግ ደካማ ኢትዮጵያን ለማየት ጓጉተው ቢሠሩም ይህ ፍላጎታቸው መቼም ሊሳካ አይችልም ብለዋል። ህወሃት የኢትዮጵያን ሕዝብ በመከፋፈል እርስ በርሱ እንዳይተማመን ሲሰራ የኖረ እኩይ ፖለቲካ አራማጅ ፀረ-ሀገር ሃይል ነው ብለዋል። ዛሬ ሴራው ከሽፎ የትግራይ ህዝብን ጨምሮ አጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ የዚህን መሰሪ ቡድን መጥፎ ተግባር ተርድቷል ብለዋል። አሁን ላይ ህወሃት ለሻዕቢያ እየተላላከና የቀድሞ ጠላቶቹን ጽንፈኛ ሸኔንና ፅንፈኛ ፋኖን አቅፎ የትላንት ክህደቱን በአደባባይ እየደገመው ይገኛልም ብለዋል። ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ በጀመረችው እድገትና ብልፅግና ወደፊት ትቀጥላለች፤ የታሪካዊ ጠላቶቿ ህልም አይሳካም ሲሉም ገልጸዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በአሁኑ ወቅት በትጥቅም በሰው ሀይል ግንባታ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በማስታወስ ለሰፈር ባንዳዎች ብቻ ሳይሆን በየትኛውም አቅጣጫ በሀገር ላይ ለሚቃጣ ጥቃት ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በአስተማማኝ ዝግጁነት ላይ መሆኑን ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የምክክር ጉባኤው የመመካከር ባህልን በማዳበር ሀገራዊ መግባባትን እያጠናከረ ነው
Aug 14, 2026 166
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በኢትዮጵያ የመመካከር ባህልን በማዳበር ሀገራዊ መግባባትን የሚያጠናክር መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ናቸው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ በህዝቦች መካከል የማይናወጥ ወዳጅነትን ለመገንባት እና በጽኑ መሠረት ላይ የተገነባች ሀገርን ለማስቀጠል ከፍተኛ ተስፋ የተጣለበት ታሪካዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ እሸቱ ኤራቦ እንዳሉት፤ የምከክር ጉባኤው ለዘመናት ማህበረሰቡ ሲያነሳቸው ለነበሩ ጥያቄዎች መፍትሄ ለመስጠት ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ ማማ ለማድረስ የሚያሰችል ነው። ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች፣ የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለማስረከብ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።   አቶ ባንቲሁን ትዛዙ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ ባህላዊ የእርቅና የመመካከር እሴት እንዲያንሰራራ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። ምክክሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ማዕዘናት የመጡ ማህበረሰቦችን በአንድ ጥላ ስር በማገናኘት የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ትስስር ለማጠናከር ማስቻሉን አብራርተዋል። ሀሳቦችን በነጻነት ወደ መድረክ ማምጣትና በግልጽነት መነጋገር ለዘላቂ ሰላምና ግንባታ ትልቅ መሰረት መሆኑን የገለጹት ደግሞ አቶ ዘሪሁን ገብረእግዚአብሔር ናቸው።   ተመካካሪዎቹ በሰፊ የቡድን ውይይቶች ያነሷቸው ነጥቦች ሀገራዊ አጀንዳዎችን በስፋትና በጥልቀት ያቀፉ በመሆናቸው፣ ሂደቱ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።  
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ ነው
Aug 14, 2026 176
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት አቀራረብ ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ መሆኑን የኢትዮጵያ የሕዝብ ዲፕሎማሲ ኢንስቲትዩት ፕሬዚዳንት ያሲን አሕመድ ገለጹ። የኢንስቲትዩቱ ፕሬዚዳንት ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በፖለቲካ መሪዎችና በመንግሥት መካከል ከሚደረጉ ምክክሮች በተለየ ወደ ሕዝብ በመውረድ ከታች ወደ ላይ የመጣ ሂደት ነው። በአፍሪካ በርካታ ሀገራት የሚካሄዱ ሀገራዊ ምክክሮች የሕዝብን ስጋትና ምኞት በማያንጸባርቅ መልኩ በመሪዎች ደረጃ በሚደረሱ ስምምነቶች ተጀምሮ ለሕዝብ የሚቀርቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የምክክር ጉባኤ ግን ከታችኛው የማኅበረሰብ ክፍል ጀምሮ የሕዝብ ተሳትፎንና አካታችነትን በማረጋገጥ ወደ ብሔራዊ ደረጃ የሚሸጋገር ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በምክክር ጉባኤው የታደሙ የተለያዩ የማኅበረሰብ ተወካዮች ስብጥርና ተሳትፎም የምክክሩን አሳታፊና አካታችነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤውም የዜጎችን ስጋቶችና ቅድሚያ የሚሰጧቸውን ዐበይት አጀንዳዎች በመለየት ወደ ብሔራዊ አጀንዳ ለማምጣት ያለመ ወሳኝ መድረክ መሆኑን አብራርተዋል። ይህም በዘመናዊት ኢትዮጵያ የሀገር ግንባታ ሂደትና ታሪክ ውስጥ ሁሉንም ዜጎች ማዕከል በማድረግ በተቋማዊና ፖለቲካዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መቀራረብን የሚገነባ አቀራረብ መሆኑን አስረድተዋል። የምክክር ጉባኤው ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ያላትን ሕብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን የዘመናት ውስብስብ ጉዳዮች በሰለጠነ የምክክር መድረክ ለመመልከትና የጋራ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያግዝ ጠቁመዋል። በሰለጠነ ዓለም ውስጥ የትጥቅ ትግል ቁርሾንና መቃቃርን የሚያባብስ እንጂ ሰላምን የሚያመጣ አይደለም ያሉት ያሲን አሕመድ፤ በመርህ ላይ የተመሠረተ ምክክር ለዘላቂ ሀገር ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአመፅና አዋኪ የትጥቅ ትግል ሀገርን በማጎሳቆል የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት፣ የዕድገትና የልማት ፍላጎት ከማቀጨጭ ያለፈ አንዳች ፋይዳ እንደሌለው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ አካታችና አሳታፊ የምክክር ጉባኤም የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማጎልበት በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመገንባት እንደሚረዳ አብራርተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ በፓርላማ በጸደቀ ሕግ መሠረት የተቋቋመና በነጻ ኮሚሽን የሚመራ መሆኑም ለምክክር ጉባኤው ሂደት ተቋማዊና ሕጋዊ መሠረት መስጠቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ከታች ጀምሮ የመጣበት አቀራረብም ልዩነቶችን ለማስተዳደር፣ መግባባትን ለመገንባትና ዘላቂ የፖለቲካ መፍትሔ ለማስገኘት ጠቃሚ ተሞክሮ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አካታችና አሳታፊነት አቀራረብ ሀገራዊ መግባባትን መገንባት ለሚሹ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተመራጭ መንገድ መሆኑን አስረድተዋል።
የግብፅ ሚዲያዎች ስለ ህዳሴ ግድብ ከራሳቸው ባለሙያዎች ሳይንሳዊ ግኝቶች ጋር የሚቃረን ዘገባ እያቀረቡ ነው-ጋዜጠኛና ፀሐፊ ዛሂድ ዚዳን
Aug 14, 2026 224
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ):- የግብፅ ሚዲያዎች ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሚያቀርቧቸው ዘገባዎች ወጥነት የሌላቸው እና ከበርካታ የግብፅ ሳይንቲስቶችና የውሃ ባለሙያዎች ሳይንሳዊ ግምገማዎች ጋር የሚጋጩ መሆናቸውን ጋዜጠኛና ፀሐፊ ዛሂድ ዚዳን ገለጹ። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡት ዛሂድ፤ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ የሚደረጉ ክርክሮች በሳይንሳዊና ቴክኒካዊ ትንተናዎች ላይ ከማተኮር ይልቅ አሻሚና እርስ በእርስ በሚቃረኑ የመገናኛ ብዙሃን ተረኮች የሚመሩ መሆናቸውን ተናግሯል። የግብፅ የጂኦሎጂ ባለሙያ ዶክተር አባስ ሸራቂ ግድቡ በተፈጥሮው በግብፅ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደማያደርስ በግልጽ ካስረዱት የሀገሪቱ ባለሙያዎች መካከል አንዱ እንደሆኑ ጋዜጠኛው ጠቅሰዋል። ሌላኛው የግብፅ ሳይንቲስት ዶክተር ሳመህ አርማኒዮስ፤ ህዳሴ ግድብ በወንዙ ፍሰት ላይ ምንም ዓይነት የውሃ እጥረት ሳይፈጥር ኤሌክትሪክ አመንጭቶ ውሃው በቀጥታ ወደ ወንዙ የሚመለስበት የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት መሆኑን ማብራራታቸውን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የህዋ ሳይንቲስቱ ዶክተር ፋሩክ ኤል-ባዝ ግድቡ የተሻለ የውሃ አስተዳደር እንዲኖር በማድረግ የኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የሱዳንን እና የግብፅንም ጥቅም ለማስጠበቅ እንደሚረዳ ማመልከታቸውን ዛሂድ አብራርተዋል።   ጋዜጠኛው እንደ ፕሮፌሰር ሰይፍ አል-ዲን ሀማድ እና የቀድሞ የሱዳን የውሃና መስኖ ሚኒስትር ኡስማን አል-ቶም ያሉ የሱዳን ባለሙያዎችን በመጥቀስ፤ ስለ አባይ ወንዝ በሚደረጉ ውይይቶች ላይ በፖለቲካዊ ጩኸት ሳይሆን በሳይንሳዊና በተረጋገጡ ማስረጃዎች ላይ የተመሰረተ ትንተና ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ማሳሰባቸውን ገልጸዋል። አንዳንድ የግብፅ መገናኛ ብዙሃን ግድቡን በአንድ ወቅት ከጎርፍና የመሠረተ ልማት ውድመት ጋር በማያያዝ፣በሌላ ጊዜ ደግሞ የውሃ መጠን መቀነስና ድርቅ ያስከትላል በማለት የሚከሱበት መንገድ ፍጹም የሚቃረን ሀሳብ ነው ብለዋል። ዛሂድ አክለው እንደገለጹት፤ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ አደጋ ይደቅናል የሚሉ የፖለቲከኞችና የመገናኛ ብዙሃን ውንጀላዎች ፖለቲካዊ ፍላጎትን ያዘሉ እንጂ ወጥ የሆነ ሳይንሳዊ መሰረት የሌላቸው ናቸው። ይህ አይነቱ የተሳሳተ ትርክት ኢትዮጵያ ወደ ተፋሰሱ ሀገራት ከሚፈሰው የናይል ውሃ 86 በመቶ ድርሻ ካለው ከአባይ ወንዝ የተፈጥሮ ሀብቷ የመልማት መብቷን ለማደናቀፍ ለበርካታ አስርታት ሲከናወን የቆየ አካሄድ እንደሆነም ነው ያስረዱት።   አጠቃላይ የአባይ ወንዝ ዓመታዊ የውሃ መጠን በክረምቱ ወራት ወዲያው ሊታወቅ የሚችል ባለመሆኑ፣ ስለ ውሃው መጠን ቀድሞ ድምዳሜ መስጠት አይቻልም ነው ያሉት ዛሂድ። ይልቁንም የግብጽ መገናኛ ብዙሃን ከፖለቲካዊ ጩኸት በመውጣት በሳይንሳዊ ጥናቶችና በተረጋገጡ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ሚዛናዊ ዘገባ እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ በሀገራችን ጉዳይ እኩል የመሳተፍና የመወሰን ዕድልን አረጋግጦልናል
Aug 14, 2026 277
ጂንካ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ እኔ አውቅልሃለው የሚለውን አግላይ አካሄድ በማስቀረት ዜጎች በሀገር ጉዳይ እኩል የመሳተፍና የመወሰን መብታቸውን ያረጋገጠ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የበና ፀማይ ወረዳ አርብቶ አደሮች ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ የዘመናት ችግሮችን መፍትሄ በመስጠት ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምና ልማትን በማስፈን ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ጉልህ ሚና እንዳለው የታመነበት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወደማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ሀገራዊ ምክክሩን አስመልክቶ ኢዜአ በበናፀማይ ወረዳ ያነጋገራቸው አርብቶ አደሮች እንዳሉት፤ ምክክሩ ለሁሉም ዜጎች በሀገር ጉዳይ ላይ እኩል የመሳተፍና የመወሰን እድልን ከመስጠት ባለፈ የቆዩ አለመግባባቶችን በምክክር ለመፍታት ያስችላል። ከአርብቶ አደሮቹ መካከል የበናፀማይ ወረዳ የሀገር ሽማግሌ አቶ ጀሞ ቦሎቾ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ከዚህ ቀደም የመደመጥ ዕድል ላላገኘው የአካባቢው አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ጭምር የመደመጥና በሀገሩ ጉዳይ ከሌሎች እኩል ውሳኔ የመስጠት መብቱን እንዳረጋገጠለት ተናግረዋል። ቀደም ሲል የአርብቶ አደሩ አካባቢ የግጭት ቀጠና እና የሰላም እጦት በስፋት የሚስተዋልበት እንደነበረ አስታውሰው፥ በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የተለዩ አጀንዳዎች መሰል ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊያን በጋራ ቁጭ ብለው መምከራቸው ለቆዩ ችግሮችና አለመግባባቶች መፍትሄ ለማምጣት ያስችላቸዋል ያሉት የሀገር ሽማግሌው፣ የምክክሩ ውጤትም ለአካባቢያቸውም ተጨባጭ ውጤት ያመጣል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል። ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርብቶ አደር ጋርሾ ማያ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ተሳታፊዎች አካታች በሆነ መንገድ የተመረጡ እና የእነሱም ወኪሎች የተገኙበት መሆኑንን ገልጸዋል።   ይህም ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች በምክክሩ እንዲደመጡና በሀገር ጉዳይ የመወሰን መብት እንዲኖራቸው ያደርጋል ብለዋል። እንደ አርብቶ አደር ጋርሾ ገለጻ፣ የምክክር ሂደቱ ሁሉንም ማህበረሰብ በየደረጃው ያሳተፈ እና የሁሉም ሀሳብ የተካተተበት ስለሆነ ለሀገር ዘላቂ ሰላምና እድገት መረጋገት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ በሀገራዊ ምክክር ኮሚሸን ተለይተው ውይይት እየተደረገባቸው ያሉ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችም በየአካባቢው የሚነሱ ፍላጎቶችን ያማከሉ እንደሆነ ጠቅሰው፣ በአጀንዳዎች ላይ የሚደረስበት መግባባትም ሀገራዊ አንድነትን ከማጠናከር ባለፈ ለሁሉም ምቹ የሆነች ሀገር ለመገንባት ያስችላል ብለዋል። ምክክሩ ሀገርን ተብትበው ከያዙ ችግሮች በማላቀቅ ወደከፍታ ማማ የሚያወጣት ታሪካዊ ዕድል ነው ያሉት ደግሞ የወረዳው ነዋሪ አርብቶ አደር አርቲ ማያ ናቸው።   የግጭትና ያለመግባባት መንስኤዎች ተቀራርቦ የመነጋገር ዕድልን ማጣት መሆኑን ጠቁመው፣ ምክክሩ ችግሮችን ለመፍታት ብቻ ሳይሆን የመመካከር ባህልን በማሳደግ ለዘላቂ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ይህን ታሪካዊ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ለሁሉም ምቹ የሆነች ሀገር መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል። የምክክር ጉባኤው ብዙ ውጣውረዶችን አልፎ መጨረሻው ምዕራፍ ላይ በመድረሱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው፣ ምክክሩ ሁሉን በእኩል አሳታፊ መሆኑ እኔ አውቅልሃለው የሚለውን አግላይ አካሄድ አስቀርቷል ብለዋል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ባለው ዋናው የምክክር ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን የወከሉ 4 ሺህ ተመካካሪዎች በተለዩ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው
Aug 14, 2026 219
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ) ፦ የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ የተቋማት አፈፃፀምን ጨምሮ፣ የሴፍቲኔት፣ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተከናወኑ ተግባራትና ሌሎች ኢኒሼቲቮችን ገምግሟል።   የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት የበጎ ፈቃድ ተግባር የአንድነትና የሰብአዊነት ትልቁ መገለጫ ነው። ዛሬ ለአንድ ሰው የዘራነው ተስፋ ነገ ለማኅበረሰባችን የሚያፈራ ፍሬ ይሆናል፣ ዛሬ የረዳነው ወገን ነገ ሌላውን ለመርዳት የሚነሳ ዜጋ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። በጎ ፈቃድ አንድ ጊዜ የሚደረግ ተግባር ሳይሆን ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር የመልካምነት ባህል በመሆኑ ባህሉን በማዳበር ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል። በሌላ በኩል በክልሉ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የቅዳሜ ገበያዎችን ተደራሽ በማድረግ የተጀመሩ ተግባራትን ማጎልበት እንደሚገባ ገልፀዋል። ዜጎችን ከተረጂነትና ከጥገኝነት በማላቀቅ ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙ ምርታማነታቸውን በማሳደግ የተጀመሩ ተግባራትም ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ሁሉም አመራር የበኩሉን ሀላፊነት እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ የመንግስት እና የፓርቲ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በምክክር ጉባኤው እየተነሱ ያሉት ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው
Aug 14, 2026 208
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከተመካካሪዎች እየተነሱ የሚገኙ ሀሳቦች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገትና የተሻለ መጻኢ ጊዜ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ተመካካሪ አበራ አኔቦ፤ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ሀገርን ወደፊት የሚያሻግሩና የጋራ ሀገርን መገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች ከተመካካሪዎች እየተነሱ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው ምክክር ለሀገራችን ዘላቂ ጥቅም የሚያስገኝ እና ለመጪው ትውልድም መልካም አርአያ የሚሆን ታሪካዊ ጉባኤ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ይህም ለኢትዮጵያ ቀጣይነት ላለው ዘላቂ ዕድገት ምቹ ዕድል ይዞ እንደሚመጣ ታላቅ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። ተመካካሪ ወይዘሮ ኦድንጊሊ ሎ፤ አካታች እና አሳታፊ የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እጅግ አስፈላጊ በሆነ ወቅት መከናወኑን ሂደቱም የተሳካና የኢትዮጵያን የወደፊት ጉዞ የሚያስቀጥሉ መልካም አጋጣሚዎችን መፍጠሩን ተናግረዋል። ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ኢትዮጵያውያንን በተወካዮቻቸው በምልዓተ ያሳተፈ መሆኑንና ኢትዮጵያን አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስችሉ ጠቃሚ ሀሳቦች በነጻነት እንዲነሱ ምቹ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሀገሪቱን ብዝሃነት ያንጸባረቀ እና ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ አዎንታዊ የምክክር ጉባኤ እንደሆነም ነው ያነሱት። ሌላኛው ተመካካሪ ​ታደሰ ዳኜ በበኩላቸው፤ ለሀገር አንድነት ምክክር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝና መልካም ውጤት ይዞ ይመጣል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል። ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች የወከሉ ተመካካሪዎች በነጻነትና አሳታፊ በሆነ መልኩ እየተመካከሩ በመሆኑ ሀገራዊ ምክክሩ ውጤታማ ነው ብለዋል።
የምክክር ጉባኤው የዘመናት ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት ነው-ተመካካሪዎች 
Aug 14, 2026 213
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታትና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ የጋራ የመፍትሔ ሀሳቦች የቀረቡበት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በምክክሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የወከሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች፤ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የጋራ የመፍትሔ ሀሳብ የቀረበበት መሆኑን ተናግረዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አቶ ነኢ አለልኝ ምክክሩ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግር ጠቃሚ ግብአቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በሀገሪቱ ለዘመናት የዘለቁ ችግሮች ላይ በስፋት ተመካክረን የመፍትሔ ሀሳቦችን አስቀምጠናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ኒሽራ ሱሌይማን ሀሳባችንን በነጻነትና በግልጽ በማቅረብ የመፍትሄ ሀሳቦች ላይ ምክክር እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። ምክክሩ መግባባት የሰፈነባት ያደገችና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ምክክሩ ለሀገር የሚበጁ ጠቃሚ ግብዓቶች የተገኙበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ደራራ ጣፋ ናቸው።
ማህበራዊ
በድሬዳዋ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማኅበራዊ ተቋማት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Aug 14, 2026 148
ድሬደዋ ፣ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፡-በድሬዳዋ አስተዳደር በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለትምህርት ቤቶችና ማኅበራዊ ተቋማት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተመላከተ። የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶችን ለግሷል፤ በመቄዶንያ የአረጋውያን መርጃ የድሬዳዋ ማዕከልም ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር አከናውኗል።   በወቅቱም የጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ጽጌረዳ ክፍሌ እንደተናገሩት፤ ቢሮው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከመሳተፍ ባሻገር በሁሉም የገጠርና የከተማ ወረዳዎች በሚገኙ አደባባዮች ከ30 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነዋሪዎች ነፃ ምርመራና ሕክምና እየሰጠ ይገኛል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጤናማ ማኅበረሰብን ለመፍጠርና ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በአንድነት መፍታት እንደሚቻል እያረጋገጠ መሆኑንም አስረድተዋል።   ቢሮው ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶችን የለገሰ ሲሆን፤ ለመቄዶንያ የአረጋውያን መርጃ የድሬዳዋ ማዕከልም ማዕድ ማጋራቱን ተናግረዋል። ቢሮው ከለገሳቸው የመማሪያ ቁሳቁስ በተጨማሪ ከቢሮው ሠራተኞች የተሰበሰቡ በርካታ አልባሳትን ለመቄዶንያ የድሬዳዋ ማዕከል መለገሱንም ገልጸዋል።   የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ በበኩላቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በእርስ መረዳዳትና መደጋገፍ ባህልን በማጠናከር ማኅበራዊ ችግሮችን በራስ አቅም የመፍታት ተቋማዊ አቅም ፈጥሯል ብለዋል። በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተለያዩ የሴክተርና የግል ተቋማት የተለያዩ የትምህርት መማሪያ ግብዓቶችን እየደገፉ መሆኑን አንስተዋል። ድጋፉን በማጠናከር አንድም ዕድሜው ለትምህርት የደረሰ ሕፃን ከትምህርት ገበታው እንዳይለይ በማድረግ የነገዋን ታላቅ ሀገር መገንባት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑንም አስምረውበታል። ዛሬ የጤና ቢሮ ያደረገው ድጋፍም የመረዳዳት እሴቱ መጠናከር ማሳያ መሆኑን ገልጸው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።    
ወጣቱ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ምክንያታዊና በእውቀት ላይ የተመሰረተ አስተሳሰብ በመያዝ እድገትን ማፋጠን አለበት
Aug 14, 2026 148
ጎንደር፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፡-ወጣቱ ለሀገር ዘላቂ ሰላም ግንባታና ልማት ወሳኝ ኃይል ከመሆን ባለፈ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ምክንያታዊና በእውቀት ላይ የተመሰረተ አስተሳሰብ በመያዝ እድገትን ማፋጠን እንዳለበት የሰላም ሚኒስቴር ገለፀ። በጎንደር ከተማ ዓለም ዓቀፍ የወጣቶች ቀን "ብዝሀ የወጣቶች እውቀት ለጋራ ትልም" በሚል መሪ ሃሳብ ተካሄዷል። በሰላም ሚኒስቴር የብቃትና የሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኮሪ አብደላ በመድረኩ እንዳሉት፤ ወጣቱ ለሰላም ግንባታና ሀገራዊ ልማት ወሳኝና አሻጋሪ ኃይል መሆን አለበት።   ከዚህም ባለፈ በማንኛውም ሀገራዊ ጉዳይ ላይ በእውቀትና በክህሎት የታገዘ ምክንያታዊ አስተሳሰብን በማዳበር ሀገራዊ እድገትን በማፋጠን ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል። ሰላም ሚኒስቴር ወጣቱን በማሳተፍ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰላምን በዘላቂነት ለማጽናት ሁሉም በጋራ መተባበር እንዳለበት አሳስበዋል። የጎንደር ከተማ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉቀን ጌታሁን በበኩላቸው የወጣቱን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።   በከተማው በሚካሔዱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ወጣቶች በተለያዩ የልማት መስኮች በንቃት እየተሳተፉ እንደሆነ ገልጸው፣ ይህም ወጣቱ ሀገራዊ ግዴታውንና ሀላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ያሳያል ብለዋል። የወጣቱን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም በግብርና፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች እንዲሳተፍ እየተደረገ ነው ያለው ደግሞ የአማራ ክልል ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወጣት አንተነህ ገብረሚካኤል ነው። ወጣቶች ዲጂታል ቴክኖሎጂን ለሰላምና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ማዋል እንዳለባቸው ገልጾ፣ መንግስት ባመቻቸው የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በመሳተፍ ያገኙትን የቴክኖሎጂ እውቀት ለገቢ ምንጭ እንዲያውሉ መክሯል። በመድረኩ ከሰላም ሚኒስቴር ተወካዮች በተጨማሪ የከተማው አመራሮችና ወጣቶችም ተሳታፊ ሆነዋል።  
የበጎ ፈቃድ ተግባር ለተተኪው ትውልድ የሚሻገር አሻራ የሚያስቀምጥ ተግባር ነው
Aug 14, 2026 181
ሰመራ፣ ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ) ፡-የበጎ ፈቃድ ተግባር የማህበረሰቡን የመደጋገፍ እሴት ከማጎልበት ባለፈ፣ ለተተኪው ትውልድ የሚሻገር አሻራ የሚያስቀምጥ ተግባር መሆኑን የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ያሲን ሐቢብ ገለጹ። ቢሮው በዛሬው ዕለት ድጋፍ ለሚሹ ከ500 በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶችንና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን እገዛ አድርጓል።   በድጋፍ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ያሲን ሀቢብ እንደገለጹት፤ የተደረገው እገዛ ሀገራዊ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል ነው። እገዛው በክልሉ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሻገር የመጣውን የመረዳዳት ባህል ከማጠናከሩ ባሻገር፣ ነገ ሀገር በሚረከበው ትውልድ ላይ ዘላቂ አሻራ የሚያስቀምጥ መሆኑን አብራርተዋል።   ድጋፍ የሚሹ ተማሪዎችን በመለየት ከ500 በላይ ለሚሆኑት የትምህርት ቁሳቁስ መሰጠቱን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ለዚህ ተግባር 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ መደረጉን ገልጸዋል።" የተደረገው ድጋፍ ቦርሳ፣ ደብተር እና እስክርቢቶ የሚያካትት ሲሆን፣ ለሴት ተማሪዎች ደግሞ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ጭምር ያካተተ መሆኑን አስረድተዋል። በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት በጤና ሚኒስቴር የሆስፒታል ዲያግኖስቲክ ዴስክ ከፍተኛ ባለሙያ ሲስተር ጥሩወርቅ አክሌ በበኩላቸው፤ የክልሉ ጤና ቢሮ ያደረገው ድጋፍ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተደረጉት ተግባራት መካከል ይህ እገዛ ተማሪዎችን ለትምህርት የሚያነቃቃና ወላጆችን ደግሞ ከወጪ የሚያድን መሆኑን አብራርተዋል። ቢሮው ያደረገው ድጋፍ የማህበረሰቡን የመደጋገፍ ባህል የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ፣ በሰዎች መካከል በሚደረግ እገዛና ማጋራት መልካም ተሞክሮ የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለት የድጋፉ ተጠቃሚ የሆኑት ተማሪዎቹ ዘሐራ አደን እና ፋጡማ ዓሊሚራህ በበኩላቸው፤ በተደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እጅግ መደሰታቸውን ገልጸዋል።  
በኦሮሚያ ክልል የሴቶችን ተሳትፎ በማሳደግ ረገድ በተከናወኑት ተግባራት ተጠቃሚነታቸው እየተረጋገጠ ነው
Aug 14, 2026 137
አዳማ ፤ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ) ፡-በኦሮሚያ ክልል የሴቶችን ተሳትፎ በማሳደግ ረገድ በተከናወኑት አበረታች ተግባራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እየተረጋገጠ መሆኑን የክልሉ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። በኦሮሚያ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ አስተባባሪነት በየደረጃው ያሉ የዞንና የከተማ አስተዳደሮች ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ሴክተር አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት መድረክ በአዳማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።   የኦሮሚያ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ መሰረት ባጫ በተለይ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ የሴቶችን ተሳትፎ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ተስፋ ሰጪ ስራዎች አከናውነዋል። በዘንድሮው ዓመት 'የእናቶችን ቤት እንገንባ' በሚል መሪ ሐሳብ፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ ባለድርሻ አካላትንና በየደረጃው የሚገኙ የሴቶች አደረጃጀቶችን በማስተባበር የ156 ሺህ ቤቶች ግንባታና ጥገና ተጠናቆ ርክክብ መፈጸሙን ለአብነት አንስተዋል። ቤቶቹ አቅመ ደካሞችና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሴቶች የተሻለና ዘላቂ መኖሪያ እንዲያገኙ ያስቻሉ ከመሆኑም በላይ፣ ማህበራዊ ችግሮቻቸውን ለመቅረፍ ማስቻላቸውን ገልጸዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የመኖሪያ ቤት ችግርን ከመቅረፍ ጎን ለጎን ሴቶችን በኢኮኖሚ ለማጠናከርና ለማብቃት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ሴቶችን በማህበር በማደራጀት በዶሮ፣ በወተት ላምና በበግና ፍየል እርባታ እንዲሁም በእንስሳት ማድለብና በሌሎችም ሥራዎች እንዲሰማሩ መደረጉንም አመልክተዋል። በተጨማሪም በክልሉ ገጠራማ አከባቢዎች የሚኖሩ ሴቶች በማህበር ተደራጅተው የእህል ወፍጮ ኢንዱስትሪ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል ብለዋል። በተመሳሳይ የሴቶችን የውሳኔ ሰጪነትና የፖለቲካ ተሳትፎ ለማጎልበት በተደረገው ጥረት፣ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጭነትና በተመራጭነት የተሻለ ተሳትፎ ማድረጋቸውን ወይዘሮ መብራት ገልጸዋል። አክለውም መድረኩ በአዲሱ የሴቶች ተጠቃሚነት ፖሊሲ ላይ ግንዛቤ በመፍጠር፣ ሁለንተናዊ ተሳትፎአቸውንና የኢኮኖሚ አቅማቸውን ለማጎልበት በተቀናጀ መልኩ ለመረባረብ የሚያስችል የጋራ አረዳድ ለመያዝ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።   የጂማ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ጫልቱ አወል በበኩላቸው፣ በዘንድሮው ዓመት የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም መመዝገቡን ገልጸዋል። ለአብነትም ከ80 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሴቶች የብድር አገልግሎት ተመቻችቶላቸው በተለያዩ የገቢ ማስገኛ መስኮች በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸው ተናግረዋል። ሴቶቹ በዋናነት በሩዝ፣ በአቮካዶ፣ በሙዝና ቅመማ ቅመም ልማት፤ እንዲሁም በማር፣ በዶሮና በወተት ላሞች እርባታ ዘርፍ በመሳተፍ ውጤታማና ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የሴቶችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለማቃለል ከአምስት ሺህ በላይ ቤቶች ተገንብተው መተላለፋቸውን ገልጸዋል። ከ300 በላይ የእንጀራ ምጣዶች፣ የዳቦ መጋገሪያ ማሽኖችና የእህል ወፍጮዎች ድጋፍ በማድረግ፣ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሴቶች በአማራጭ የገቢ ምንጮች ተሰማርተው ራሳቸውን በዘላቂነት እንዲችሉ መደረጉንም ተናግረዋል።   የምስራቅ ወለጋ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ አልማዝ ሞሲሳ በዞኑ የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ከጥገኝነት ለማላቀቅ በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም ለአቅመ ደካሞችና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ሴቶች የሚሆኑ ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሴቶች ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ መስኮች እንዲሰማሩ መደረጉን በመጠቆም፣ በተለይም በግብርና፣ በአነስተኛ ንግድና የአገልግሎት ዘርፎች እንዲሳተፉ የተለያዩ ድጋፎችና እገዛዎችን በማድረግ ረገድ ውጤታማ ሥራ መከናወኑን አመልክተዋል።    
ኢኮኖሚ
ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ በማድረግ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ለውጥ ማምጣት ተችሏል
Aug 14, 2026 253
ሐዋሳ፤ ‎ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ በማድረግ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት መቻሉን የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ለወጣቶች ቀጣይነት ያለው የሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮግራም ''SEED'' በሲዳማ ክልል የሦስት ዓመት የሥራ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫ ላይ የሚመክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሄዷል፡፡   የሲዳማ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት በማብቃት በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት ተችሏል፡፡ ከዚህ ቀደም የነበረው የሥራ ዕድል ፈጠራ ክህሎት መር ባለመሆኑ የተነሳ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ውጤታማ አለመሆን የዘርፉ ፈተና ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል። ዘርፉ በዜጎች ክህሎትና አመለካከት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን እንደ ሀገር አቅጣጫ ተይዞ መሥራት ከተጀመረ በኋላ፤ በተለይ ወጣቶች በተሻለ አቅምና ፍላጎት ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡   በዚህም ውጤታማ የሆኑና ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሥራ ዕድል መፍጠር የቻሉ በርካታ ወጣቶችን ማፍራት እንደተቻለ ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ከፍተኛ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የቢሮው ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ በበኩላቸው፤ አጋር አካላትን ከሥልጠና ተቋማት ጋር በማቀናጀት የክህሎት ክፍተቶችን የመሙላት እና ወደ ሥራ የሚገቡትን የማብቃት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   ቅድሚያ ለክህሎትና አመለካከት በመስጠት የፋይናንስ፣ እንዲሁም የመሥሪያና የመሸጫ ቦታዎችን የማቅረብ ሥራ እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲቲዩት የሲዳማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የደቡብ ኢትዮጵያና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሎች አስተባባሪ አቶ ጌትነት ሳሙኤል፤ በኢንስቲትዩቱ የሚመራው የሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮግራም በአምስት ዓመታት ውስጥ ለ1 ሚሊዮን ወጣቶች ቀጣይነት ያለው የሥራ ዕድል የመፍጠር ዕቅድ አለው ብለዋል፡፡   ፕሮግራሙ ከተመረጡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ጋር በመሆን የክህሎት ሥልጠና የመስጠት፣ እንዲሁም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የብድር አቅርቦት የማመቻቸት ሥራ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡ በፕሮግራሙ በሲዳማ ክልል በሦስት ዓመታት ውስጥ ከ27 ሺህ በላይ ወጣቶች የክህሎት ሥልጠና ያገኙ ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥ ከ19 ሺህ በላይ የሚሆኑት የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው አብራርተዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመቀናጀትም ለኢንተርፕራይዞች ከ181 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር እንደተሰራጨ ጠቁመዋል፡፡   በፕሮግራሙ ድጋፍ ካገኙ ኢንተርፕራይዞች መካከል የጠይም ጋርመንት አባል የሆነችው ወጣት ቤርሳቤህ አለማየሁ እና የጃዋታ ጨርቃ ጨርቅ ማኅበር አባል የሆነችው ወጣት ራህመት ሁሴን፤ በፕሮግራሙ ባገኙት ሥልጠና ከዚህ ቀደም የነበረባቸውን የሂሳብ አያያዝና ሌሎች ክፍተቶች በመሙላት በሥራቸው ትርፋማ መሆን እንደቻሉ ገልጸዋል፡፡   በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል፡፡  
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚወስዱበት ነው
Aug 14, 2026 276
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚወስዱበት መሆኑን በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ሕብረት የሳህራዊ ሪፐብሊክ አምባሳደር ላሚን ባአሊ ገለጹ። አምባሳደር ባአሊ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በሌሎች ዘርፎች ስኬታማ ጉዞ እያደረገች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ስኬታማ ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንም አንስተዋል። ይህ ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ዜጎች የፖለቲካ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ አዎንታዊ ማረጋገጫ እንደሆነም ነው የተናገሩት። በምርጫው የፖለቲካ ፓርቲዎች በንቃት መሳተፋቸውን በመጥቀስ፣ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ውስጥ በጎ እርምጃ መሆኑንም አምባሳደር ባአሊ አስረድተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው የሪፎርም አጀንዳ በሀገሪቱ ውስጥ ለበለጠ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ልማት ዕድገት አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በተጣጣመ መልኩ የሚከናወኑ የተለያዩ የልማትና የለውጥ ሥራዎች አዎንታዊ ውጤት እያመጡ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። በሀገሪቱ እየተተገበረ ያለው የኢኮኖሚ ሪፎርም የዜጎችን ኑሮ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ጨምረው አንስተዋል፡፡ ይህ በኢትዮጵያ እውን እየሆነ ያለው ውጤታማ ሪፎርም በዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትና እውቅና ማግኘቱን ተናግረዋል። በመሆኑም ይህ የኢትዮጵያ ስኬታማ ተሞክሮ በአጠቃላይ በአፍሪካ ደረጃ የሚገኙ ሌሎች ሀገራት ትምህርት ሊወስዱበት የሚችል ነው ብለዋል። ሀገራዊ ምክክር አስፈላጊ የፖለቲካ ልምምድ እንደሆነ የጠቆሙት አምባሳደሩ፣ በኢትዮጵያ እየተደረገ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ለሁሉም አካላት ዘላቂ ጥቅም ለማስገኘት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል። በሳህራዊ ሪፐብሊክ እና በኢትዮጵያ መካከል እ.ኤ.አ ከ1970ዎቹ ጀምሮ የነበረውን ትብብር አውስተው፣ የሀገራቱ ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰዋል። ባህል፣ ስፖርት፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ጤና እና ሌሎች የጋራ ፍላጎት በሆኑ ዘርፎች የሁለትዮሽ ትብብሩን የበለጠ ለማስፋት እንደሚሰራም አምባሳደር ላሚን ባአሊ ገልጸዋል።
በድሬደዋ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ነው
Aug 14, 2026 218
ድሬደዋ፣ ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ)፡- በድሬደዋ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ተናገሩ። በድሬዳዋ "ከሥራ ጠባቂነት ወደ ሥራ ፈጣሪነት" በሚል መሪ ሐሳብ የወጣቶችን ሥነ-ልቦናዊ የሥራ ላይ ብቃት የሚያጠናክር ሥልጠና እየተሰጠ ነው።   በወቅቱም በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እንደተናገሩት፤ የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ነው። በአስተዳደሩ ገጠርና ከተማ የሚገኙ ወጣቶችን በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሠሩ የሚገኙ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በመተግበር ላይ የሚገኘው "ብቃት የሥራ ላይ የወጣቶች ሥልጠና" ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ አበርክቶው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።   ለአራተኛው ዙር የተመለመሉ ወጣቶች የተፈጠረላቸውን የሥራ ዕድል በመጠቀም ራሳቸውንና ሀገራቸውን ለመለወጥ በቁርጠኝነት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፤ ባለፉት ሦስት ዙሮች የሥራ ላይ የሥልጠና መርሃ-ግብር ከ2 ሺህ 900 በላይ ወጣቶችን የሥራ ባለቤት ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። በዚህም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች እና ተቋማት ጋር በማስተሳሰር የሥራ ላይ ክህሎትና ዕውቀት እንዲቀስሙ የተሰራው ስራ ውጤታማ ነበር ብለዋል።   የዛሬ ተመልማዮችም ከተቋምና እና ኢንዱስትሪዎች ጋር በመተሳሰር የ6 ወራት የሥራ ላይ ብቃታቸውን በማረጋገጥ የሥራ ባለቤት እንደሚሆኑም ጠቁመዋል። ዘንድሮም ለአራተኛ ዙር ሥልጠና የተመለመሉ 1 ሺህ 800 ወጣቶች በአስተዳደሩ ሁለት የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መሠረታዊ ክህሎት መር ሥልጠና ተሰጥቷቸው ለሥራ ላይ ልምምድ ዝግጁ መደረጋቸውን ገልጸዋል። በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ለወጣቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ያሳየውን ቁርጠኝነት የፌደራል መንግሥት በማረጋገጡ በየዓመቱ ተጠቃሚ ሲደረጉ የነበሩ ወጣቶችን ቁጥር ከ970 ወደ 1 ሺህ 800 ከፍ እንዲል ማድረጉን አስረድተዋል። የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ከሆኑት ወጣቶች መካከል ወጣት በአምላክ አምሳሉ እና ወጣት አፈንዲ ሙሳ፤ የተፈጠረላቸውን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ራሳቸውንና ሀገራቸውን ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።    
የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ኢትዮጵያን ከገናና የዕድገት እና ሥልጣኔ ታሪኳ ጋር የማስታረቅ የሕልውና ጉዳይ ነው
Aug 14, 2026 294
አዲስ አበባ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ኢትዮጵያን ከገናና የዕድገትና ሥልጣኔ ታሪኳ ጋር የማስታረቅ የሕልውና ጉዳይ መሆኑን በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ቀንድ እና የውኃ ጂኦፖለቲካ ከፍተኛ ተመራማሪ ጋሻው አይፈራም (ዶ/ር) ገለጹ። ጋሻው አይፈራም (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት ከገናና ሥልጣኔዋ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ የባሕር በር ባለቤት እንደነበረች አስታውሰዋል። በአክሱም ሥልጣኔ ወቅትም ሆነ ከዚያ በፊትና በኋላ በነበሩት ዘመናት፣ ኢትዮጵያ የንግድና የውጭ ግንኙነቷን በቀይ ባሕር ቀጣና በባሕር በርና የወደብ አገልግሎቶች አማካኝነት ታሳልጥ እንደነበር ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ለማሳጣት የውስጥ እና የውጭ ባዕዳን ኃይሎች በየዘመናቱ ያልሸረቡት ሴራና ያልፈነቀሉት ድንጋይ እንዳልነበርም አስረድተዋል። ታሪካዊ ጠላቶች የሚሸርቡትን ሴራ በመመከትና በማክሸፍ፣ ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባሕር በር ባለቤትነቷን ለሺህ ዘመናት አስጠብቃ መቆየቷን አብራርተዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድንና የሻዕቢያ ስብስብ ያለምንም ተጨባጭ ማስረጃም ሆነ አመክንዮ ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። በዚህም ኢትዮጵያን ከገናና ታሪክና ሥልጣኔዋ ጋር በእጁጉ ከተቆራኘው ቀይ ባሕር እንድትገለል መድረጉን አመልክተው፤ በሀገሪቷ ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው በደል መፈጸሙን አስታውሰዋል። በኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ላይ የተፈጸመው ክህደትም በሀገሪቷ ዕድገትና ብልፅግና፣ በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ላይ እንቅፋት መፍጠሩን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ባሕር በር አልባነት ከሀገሪቷ የንግድና የሎጂስቲክስ አቅም ጋር ተያይዞ በገቢና ወጪ ንግድ ላይ ከፍተኛ የወደብ ኪራይና ሌሎች የገንዘብ ወጪዎችን እንድታወጣም እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በሌላ መልኩም በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የሚንቀሳቀሱ የሽብር ኃይሎች የሚፈጥሩትን የሰላምና ደኅንነት ስጋት ለመመከት ከባሕር በር ባለቤትነት መገለሏ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ቀላል የሚባል እንዳልሆነ ገልጸዋል። በዚህም የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የትውልድን መጻኢ ዕጣ ፈንታ የሚወስን የብሔራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄው የታሪክ ስብራትን የማረምና ኢትዮጵያን ከገናና ታሪክና ሥልጣኔዋ ጋር የማስታረቅ ጉዳይም ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርን በማጠናከር የአፍሪካን ኢኮኖሚ ውህደት ለማሳለጥ በምታደርገው ጥረት የባሕር በር ባለቤትነትን ጥያቄውን ምላሽ ማስገኘት እንደሚያስፈልግ አስረጂ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ቀጣናዊ ሰላምና ደኅንነት፣ የጋራ ዕድገትና ብልፅግናን ማረጋገጥ የዚህ ትውልድ ሀገራዊ ኃላፊነት መሆኑንም አስገንዝበዋል። የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄው ዓለም አቀፍ ቅቡልነት እያገኘ ነው ያሉት ምሁሩ፤ ለዚህም ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ ተቋማትና መገናኛ ብዙኅን የጉዳዩን አስፈላጊነት በቅጡ መገንዘባቸውን አብራርተዋል። በቀጣይም በጋራ ተጠቃሚነት መርህ የሚደረጉ የዲፕሎማሲ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ መክረዋል። ለዚህም ኢትዮጵያውያን በሁሉም መስክ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄውን በበለጠ በማስገንዘብ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ በትብብር መሥራት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ ናቸው
Aug 14, 2026 182
አዳማ ፤ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ )፡- በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ መሆናቸውን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ገለፁ። በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የተመራ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በአዳማ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የዲጂታል መሰረተ ልማትና ሌሎች የልማት ስራዎችን ገብኝቷል።   በዚህ ወቅት አቶ ጥራቱ በየነ እንደገለጹት፤ በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ ናቸው። "ከዚህ ቀደም ልምድ ለመቅሰም ወደ ውጭ ሀገር ከተሞች እንሄድ ነበር፤ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ግን በሀገር ውስጥ ከተሞች ከቴክኖሎጂ ልማትና አጠቃቀም፣ ከአገልግሎት ዲጂታላይዜሽንና መሠረተ ልማት ዝርጋታ አንጻር ልምድና ዕውቀት መቅሰም እየቻልን ነው" ብለዋል። በተለይ በአዳማ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥን ከማዘመን እና የጸጥታና ደኅንነት አሠራሮችን ዘመናዊ ከማድረግ አኳያ የተሰሩ ሥራዎች ጥሩ ተሞክሮ የሚወሰድባቸው እንደሁኑ ገልጸዋል። በተመሳሳይም በትራንስፖርት ስምሪትና በትራፊክ ቁጥጥር ሥርዓት፣ ቴክኖሎጂን በማላመድና አገልግሎት ላይ በስፋት በማዋል ረገድ ጥሩ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።   በተለይ የመሬት ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደርና ለሕዝብ ልማት በማዋል ረገድ የአዳማ ከተማ አስተዳደር የመሬት ካዳስተር ሥርዓት በማሳያነት ሊጠቀስ የሚችል መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። በከተማ ግብርና፣ የአርሶ አደሩን ሕይወትና የአኗኗር ዘይቤ ለማዘመንና ከተማዋ አርሶ አደሩን በማቀፍ ዕድገቷ እንዲቀጥል የአርሶ አደሮች ሞዴል መንደር ልምድ የተገኘበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም አርሶ አደሩ የተሟላ መሠረተ ልማት በአንድ ቦታ እንዲያገኝ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባው አክለውም ከአዳማ ከተማ የተገኘውን ተሞክሮ በከተማቸው ካለው አተገባበር ጋር በማቀናጀት ወደ ውጤት እንደሚቀይሩትም ተናግረዋል። የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው፤ በከተማዋ በተከናወነው የመሠረተ ልማት ዝርጋታና አገልግሎትን በማዘመናችን አዳማ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንድትሆን ሰፊ ዕድል እየፈጠረ ነው ብለዋል። የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመንና በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የተገልጋዩን እርካታ ማረጋገጥ መቻሉንም ገልጸዋል። በአዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ለማዘመን የተሠራው ሥራ ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል። በዚህም የመሬት ሀብቱን በአግባቡ በማስተዳደር ከሌብነትና ምዝበራ መታደግ መቻሉን፣ የከተማዋ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን፣ ሕዝቡ በከተማዋ ልማት እያደረገ ያለው ተሳትፎ እንዲጨምርና እንዲጠናከር ማስቻሉንም ጠቁመዋል።    
በመሶብ የአንድ ማዕከል ያገኘነው ቀልጣፋ አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ጊዜያችንን ለመቆጠብ አስችሎናል
Aug 14, 2026 100
ሀዋሳ ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦ በሃዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል ያገኘነው ቀልጣፋ አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ጊዜያችንን ለመቆጠብ አስችሎናል ሲሉ ተገልጋዮች ገለጹ። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የመሰሉና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፉ አሠራሮች አገልግሎትን የሚያቀላጥፉና የተገልጋይ እንግልትን የሚያስቀሩ የመደመር መንግስት እሳቤ ፍሬዎች ናቸው። አገልግሎቱ አላስፈላጊ ቢሮክራሲን በማስወገድ፣ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ እና የአገልግሎት አሰጣጥ ጊዜን ከቀናት ወደ ደቂቃዎች በማሳነስ የዜጎችን ጊዜ፣ ጉልበትና ገንዘብ እንዲቆጠብ እያደረገ ይገኛል። የሐዋሳው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የሚሰጠው ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር ከዚህ ቀደም የነበረውን የጊዜ ብክነትና እንግልት እየቀነሰ መሆኑን ተገልጋዮች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ደሳለኝ ፋንታ የተባሉ የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ የንግድ ፈቃድ ለማሳደስ ወደ ማዕከሉ መምጣታቸውን ጠቅሰው፤ በ10 ደቂቃ ውስጥ ጉዳያቸውን መጨረሳቸውን ተናግረዋል፡፡ መንግሥት ማዕከሉን ለማስፋፋት የወሰደውን ቁርጠኝነት ያደነቁት ተገልጋዩ፤ ዜጎችም ለውጤታማነቱ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸውም አመልክተዋል፡፡ የማዕከሉ አገልግሎት የተደራጀና ዘመኑን የዋጀ በመሆኑ ከዚህ ቀደም የሚስተዋሉ መጉላላቶች ቀርተው ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላኛዋ ተገልጋይ ወይዘሮ ሰላማዊት ከፈለኝ ናቸው፡፡ ለስም ዝውውርና ለንግድ ፈቃድ እድሳት መምጣታቸውን ጠቅሰው በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልጸዋል፤ የተለያዩ ተቋማት በአንድ ማዕከል ውስጥ መኖራቸው አሠራሩን ቀልጣፋ አድርጎታልም ብለዋል፡፡ አቶ ሸምሱ ተስፉ የተባሉ የማዕከሉ ተገልጋይ በበኩላቸው፤ የማዕከሉ ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር በደቂቃዎች ውስጥ የመጡበትን ጉዳይ ለመፈፀም እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡ ይህም ጊዜ፣ ገንዘብና ጉልበታቸውን እንደቆጠበላቸው ገልጸው፤ መንግሥት ማዕከሉን በማስፋፋት በአገልግሎት ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ የጀመረው ሥራ ውጤታማ መሆኑን መስክረዋል፡፡ መሶብ የተገልጋይን እርካታ ከማሳደግ ባለፈ የሠራተኛውን የሥራ ባህል የቀየረ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በማዕከሉ የሐዋሳ ከተማ መሬት አስተዳደርና ኢንቨስትመንት መምሪያ ቡድን መሪ አዛሪያስ አስማማው ናቸው፡፡   በማዕከሉ የሚሰጠው አገልግሎት የሚፈጸምበትን የጊዜ ገደብ በማሻሻልና ቅድሚያ ማግኘት የሚገባቸውን በመለየት ጭምር የተገልጋይ እርካታን ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ የሐዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ኤርሚያስ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ የሚሰጠው ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር በአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፍ ለሚታዩ ችግሮች መፍትሔን ያመጣ ነው ብለዋል፡፡   ባሳለፍነው ግንቦት ወር መጨረሻ ሥራ በጀመረው የሐዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 13 የሚደርሱ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት 57 አገልግሎቶችን እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በማዕከሉ እስካሁን ከ37 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን ገልጸው፤ ተገልጋይ ተኮር የሆነው አሰራር የተገልጋይ እርካታን እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል፡፡
የሀገር ሉዓላዊነትንና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቅ ዘመናዊ ሰራዊት ለማደራጀት ቴክኖሎጂ ወሳኝ ነው-ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Aug 12, 2026 222
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፦የሀገር ሉዓላዊነትንና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቅ ዘመናዊ ሰራዊት ለማደራጀት ቴክኖሎጂ ወሳኝ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ፡፡ የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የተደራጀ ዘመናዊ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለመገንባት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በስምምነቱ ወቅት እንደገለጹት፥ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩቱ መቋቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ የሀገርን ሉዓላዊነት እና ብሔራዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ ዘመናዊ ሠራዊት ለማደራጀት በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ መታገዝ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የኤ.አይ ቴክኖሎጂ ለመከላከያ ኃይል በተለይም በአየር፣በምድር እና በሳይበር አቅም ግንባታ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ም የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ለመደገፍ ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑንም ገልጸዋል። ሁለቱ ተቋማት በሎጂስቲክስ፣ በስልጠና፣ በሳይበር ደህንነት፣ በመከላከያ ሰራዊት ጤና አጠባበቅ፣እንዲሁም በአየር ኃይል እና በኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር ዘርፎች በኤ.አይ በመታገዝ የሠራዊቱን አቅም ማሳደግ የሚያስችሉ አበይት ጉዳዮችን ላይ መወያየታቸውን ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዞ አንዱ መገለጫ -መሶብ
Aug 12, 2026 331
(በሙሴ መለሰ) የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች መመላለስ፣ የወረቀት ክምርና ረጅም ሰልፍ የኢትዮጵያውያን የቆየ የዕለት ተዕለት ፈተና ነበር። ይህንን የዜጎች እንግልት በዘላቂነት ለመቅረፍ እና አሰራርን ለማዘመን ታስቦ የተመሠረተው መሶብ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል። የተቀናጀው የ"አዲስ መሶብ" ሱፐር አፕ (Super App) ዲጂታል መድረክ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ወደ ሙሉ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። የመሶብ ዋና ዓላማ ተበታትነው የነበሩ ልዩ ልዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ አጋዥነት በአንድ ጣሪያ ስር ማገናኘት ነው። ዜጎች ጊዜና ገንዘባቸውን ሳይባክኑ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ፣ የሰዎችን ቀጥተኛ ንክኪ በመቀነስ ሙስናና ብልሹ አሰራርን መዋጋት፣ እንዲሁም ግልጽነትን ማስፈን የተቋሙ መሠረታዊ ምሰሶዎች ናቸው። በረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ደግሞ እያንዳንዱ ዜጋ በብሔራዊ የፋይዳ (Fayda) መታወቂያው ብቻ በመጠቀም ሁሉንም የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ አካውንት እንዲያገኝ ማድረግ እና ሥርዓቱን ለአፍሪካ ሀገራት እንደ መሪ ተሞክሮ ማቅረብን ያለመ ነው። ይህ የዲጂታል መድረክ እና አጠቃላይ የቴክኖሎጂ ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሀገር በቀል እውቀት የበለጸገ ሲሆን፣ ጥቅም ላይ የዋሉት የሶፍትዌር ቴክኖሎጂዎች ለሁሉም ክፍት የሆነ (Open-source) መሆናቸው ተቋሙን ከከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ አድኖታል። በማዕከላቱ ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች ጥብቅ የሆነ የምልመላ ፈተና እና ልዩ ስልጠናዎችን አልፈው የሚገቡ በመሆናቸው የአገልግሎት ጥራቱ ከብልሹ አሰራር የፀዳ እንዲሆን አስችሏል። መጀመሪያ ላይ በ12 ተቋማትና በ41 አገልግሎቶች ብቻ የተጀመረው ይህ ዘመናዊ አሰራር፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እያሳየ ባለው ፈጣን እድገት በአሁኑ ወቅት የትስስር አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችሏል። አሁን ባለው ተጨባጭ ቁመና መሶብ 27 ዋና ዋና የመንግሥት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መስመር ማገናኘት የቻለ ሲሆን፣ እነዚህ ተቋማት በአንድ ላይ በመቀናጀት ከ288 በላይ የተለያዩ ዲጂታል አገልግሎቶችን በጥራትና በፍጥነት እያቀረቡ ይገኛሉ። ተገልጋዮች እንደ ፓስፖርት፣ ውክልና፣ የንግድ ፈቃድ እና የሰነዶች ማረጋገጫ ያሉ ወሳኝ ጉዳዮቻቸውን በአንድ ማዕከል ወይም በሞባይል መተግበሪያቸው ማከናወን ይችላሉ። ይህንን ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ100 በላይ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ማዕከላት የተቋቋሙ ሲሆን፣ እስካሁንም ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በማስተናገድ የአገልግሎት እርካታውን በፌዴራል ደረጃ ወደ ከ98 በመቶ በላይ ማድረስ ተችሏል። በቅርብ ቀናት ውስጥ የወጡ አዳዲስ ወቅታዊ መረጃዎች ደግሞ ተቋሙ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ እና ተለዋዋጭ እያደረገው መሆኑን ያሳያሉ። በቀን የሥራ ሰዓት መስተናገድ ለማይችሉ ሠራተኞችና ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ከተለመደው የሥራ ሰዓት ውጭ የምሽት አገልግሎት (Night Service) በይፋ ተጀምሯል። ከዚህ በተጨማሪ ወደ ማህበረሰቡ በቀጥታ በመሄድ አገልግሎት የሚሰጡት እና የራሳቸውን ኃይል በከፊል ከፀሐይ ብርሃን የሚያመነጩት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ አውቶቡሶች (Mobile Mesob Bus) በተለይ ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች የቤት ለቤት አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። የጤናው ዘርፍ አገልግሎቶችንም ለማካተት ከቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ጋር አዲስ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ ወደ ሀገር ለሚገቡ ባለሃብቶችና ዳያስፖራዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በቦሌ ዓለም አቀፍ አየውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ማዕከል እየተገነባ ይገኛል። በአዲስ አበባ ከተማም ከ480 በላይ የአገልግሎት መስኮቶች የሚኖሩት አንድ ግዙፍ ማዕከላዊ የኮምፕሌክስ ሕንፃ ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ ነው። “ዩኒፋይድ መሶብ” የተሰኘው የኦንላይን መድረክ ዜጎች በሞባይል ስልካቸው የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችል ሥርዓትም ተግባራዊ ሆኗል። በአሁኑ ወቅት መሶብ ከሀገር ውስጥ አልፎ ዓለም አቀፍ ትኩረትን እየሳበ ይገኛል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቤኒን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን ማዕከሉን በይፋ የጎበኙ ሲሆን፣ መሶብ ለአፍሪካ ሀገራት በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመንግሥት አገልግሎት ሥርዓት ለመገንባት እንደ ትልቅ የምርጥ ተሞክሮ ማሳያ እየተወሰደ ነው። በቀጣይም ከጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ጋር በዲጂታል አገልግሎት ዙሪያ የጋራ ትስስር በመፍጠር የአህጉር አቀፍ የዲጂታል ሥርዓት የመገንባት ስትራቴጂ ተነድፎ እየተሰራ ይገኛል። በአጠቃላይ መሶብ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን እና የሕዝብን እንግልት በመቀነስ ረገድ ውጤታማነቱን በተግባር ያረጋገጠ ስኬታማ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማሳያ ነው።
ስፖርት
ኢትዮጵያን በሶስት የአፍሪካ ዋንጫዎች የወከሉት ታዋቂው የብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፍስሐ ወልደአማኑኤል ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
Aug 13, 2026 145
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ከታዩ ታላላቅ ተጫዋቾች አንዱ የሆኑት ፍስሐ ወልደአማኑኤል ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። "ኳስ ፊደሉ" እና "ጠመንጃው" በሚሉ ቅጽል ስሞች የሚታወቁት አቶ ፍስሐ፣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ እና ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጨዋታ ዘመናቸው ከፍተኛ አገልግሎት ሰጥተዋል። ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋርም የኢትዮጵያ ሻምፒዮና እና ዋንጫዎችን አሸንፈዋል። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይም የብሔራዊ ቡድኑን ማልያ ለብሰው ተሰልፈዋል። ለከፍተኛ ትምህርት ወደ አሜሪካ አምርተው ኑሯቸውን እዚያው ያደረጉት አቶ ፍስሐ፣ ለሀገሪቱ ክለቦች ከመጫወታቸው በተጨማሪ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን (ESFNA) መስራች አባል እና ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በህልፈታቸው የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ፣ ለቤተሰብ፣ ለወዳጅ ዘመድ እና ለስፖርት ቤተሰቡ መጽናናትን ተመኝቷል።  
ፒኤስጂ የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ባለቤት ሆነ
Aug 13, 2026 274
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ መርሐ ግብር ፒኤስጂ አስቶንቪላን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በኦስትሪያ በሚገኘው ሬድ ቡል አሬና በተካሄደው ጨዋታ ክቪቻ ክቫራትስኬሊያ እና ዴዚሬ ዱዌ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። የ17 ዓመቱ ታዳጊ ብሪያን ማጆ የአስቶንቪላ ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጨዋታው አዝናኝ እና በርካታ የግብ እድሎች የተፈጠሩበት ነበር። ፒኤስጂ የአውሮፓ አሸናፊ አሸናፊዎች ዋንጫ አንስቷል። በሉሲስ ኤነሪኬ የሚመራው ፒኤስጂ ባለፈው የውድድር ዓመትም ላይ ቶተንሃምን በተመሳሳይ በመለያ ምት አሸንፎ የዋንጫው ባለቤት እንደነበር የሚታወስ ነው። የፈረንሳዩ ክለብ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ዋንጫ አግኝቷል። አስቶንቪላ ዋንጫውን በብቸኝነት ያነሳው እ.ኤ.አ በ1982 ባርሴሎናን በማሸነፍ ነበር። ከ44 ዓመት በኋላ ዋንጫውን የማንሳት ህልሙ አልተሳካም። የ34 ዓመቱን ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታን ጨዋታውን በዋና ዳኝነት መርቷል። ይህም በውድድሩ የ51 ዓመታት ታሪክ ውስጥ የአሸናፊዎች አሸናፊ ጨዋታን የመሩ የመጀመሪያው የአውሮፓ ዜግነት የሌላቸው ዳኛ አድርጓቸዋል። የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ የክለቦች ውድድር አሸናፊዎችን የሚያገናኝ የዓመቱ ማጠቃለያና አዲስ የውድድር ዘመን መክፈቻ መርሐ ግብር ነው። የጨዋታው አሸናፊው ፒኤስጂ የአምስት ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ሽልማት የሚያገኝ ሲሆን፥ ተሸናፊው አስቶንቪላ ደግሞ አራት ሚሊዮን ዩሮ ወደ ካዝናው ያስገባል።
ፒኤስጂ ከአስቶንቪላ፤ የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ፍልሚያ
Aug 12, 2026 226
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ መርሐ ግብር ዛሬ በፒኤስጂ እና አስቶንቪላ መካከል ይደረጋል። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ ኦስትሪያ በሚገኘው ሬድ ቡል አሬና ይካሄዳል። የፈረንሳዩ ፒኤስጂ ለዚህ ጨዋታ የበቃው በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ላይ አርሰናልን በመለያ ምት አሸንፎ ዋንጫውን በማንሳቱ ነው። በሉሲስ ኤነሪኬ የሚመራው ፒኤስጂ ባለፈው የውድድር ዓመትም ላይ ቶተንሃምን በተመሳሳይ በመለያ ምት አሸንፎ የዋንጫው ባለቤት እንደነበር የሚታወስ ነው። በሌላ በኩል አስቶን ቪላ በአሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ መሪነት በዩሮፓ ሊግ ፍጻሜ የጀርመኑን ፍራይበርግ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለዛሬው ጨዋታ በቅቷል። በታሪክ አስቶን ቪላ እ.ኤ.አ በ1982 ባርሴሎናን አሸንፎ ዋንጫውን አንዴ ጊዜ አንስቷል። ፒኤስጂ እና አስቶን ቪላ ከዚህ ቀደም በአውሮፓ መድረክ የተገናኙት እ.አ.አ 2024/25 የሻምፒዮንስ ሊግ ሩብ ፍጻሜ ላይ ብቻ ነበር። በወቅቱ ፒኤስጂ በሜዳው 3 ለ 1 ሲያሸንፍ፥ አስቶን ቪላ በቪላ ፓርክ የ3 ለ 2 ድል አስመዝግቧል። በድምር ውጤት ፒኤስጂ 5 ለ 4 በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜ ያለፈ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ መሆን ችሏል። ይህንን ጨዋታ ይበልጥ ልዩ የሚያደርገው በዳኝነት ረገድ የሚመዘገበው አዲስ ታሪክ ነው።   የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (ዩኤፋ) ጨዋታውን በዋና ዳኝነት እንዲመሩ የ34 ዓመቱን ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታንን መርጧል። ይህም በውድድሩ የ51 ዓመታት ታሪክ ውስጥ የአሸናፊዎች አሸናፊ ጨዋታን የመሩ የመጀመሪያው የአውሮፓ ዜግነት የሌላቸው ዳኛ ያደርጋቸዋል። የአውሮፓ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ የክለቦች ውድድር አሸናፊዎችን የሚያገናኝ የዓመቱ ማጠቃለያና አዲስ የውድድር ዘመን መክፈቻ መርሐ ግብር ነው። ጨዋታው መደበኛው 90 ደቂቃ በአቻ ውጤት ከተጠናቀቀ፥ ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ ሳይሄድ በቀጥታ ወደ መለያ ምት ያመራል። የጨዋታው አሸናፊው ቡድን የአምስት ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ሽልማት ሲያገኝ፥ ተሸናፊው ደግሞ አራት ሚሊዮን ዩሮ ወደ ካዝናው ያስገባል። የውድድሩ ስኬታማ ክለብ ሪያል ማድሪድ ሲሆን ስድስት ጊዜ ዋንጫውን አንስቷል። ባርሴሎና እና ኤሲ ሚላን በተመሳሳይ በአምስት ዋንጫዎች ይከተላሉ።
አካባቢ ጥበቃ
አረንጓዴ ዐሻራ፦ የምግብ ሉዓላዊነት ምሰሶ
Aug 14, 2026 93
(በሙሴ መለሰ) የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአፈር መሸርሸር እና የተፈጥሮ ሀብቶች መመናመን በአሁኑ ወቅት የዓለማችን ዋነኛ የህልውና ስጋቶች ሆነዋል። ኢትዮጵያም የዚህ ችግር ተጠቂ ናት። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ ተግዳሮቶቹን በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ነው። የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም፣ የደን ሽፋንን መጨመር፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት በወቅቱ አረንጓዴ ዐሻራ ሲጀመር የነበሩ አበይት አላማዎች ናቸው። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ መጀመሩ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘንድሮው ዓመት ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ መቀመጡን እና በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የምታስተናግደው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ድረስ የሀገሪቱን ግብ ወደ 65 ቢሊዮን ከፍ ለማድረግ መታቀዱን ገልጸዋል። ሐምሌ 27/ 2018 በተካሔደው የዘንድሮው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይም 800 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል ታቅዶ፣ 805 ነጥብ3 ሚሊዮን በመትከል ከእቅዱ በላይ ማሳካት ተችሏል። ከ26 ነጥብ2 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው የተሳተፉበት ይሄ መርሃ-ግብር በአጠቃላይ 294 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ነበር። በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ለመትከል ከታቀደው ስምንት ቢሊዮን ችግኞች መካከልም ከ6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ መተከሉን መረጃዎች ያሳያሉ። የአረንጓዴ ዐሻራ ከአካባቢ ጥበቃ ስራ ባሻገር ሀገራዊ የምግብ ዋስትናን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። መርሃ-ግብሩ ከተራቆቱ መሬቶች መልሶ ማገገም ባለፈ፣ በምግብ ራስን ለመቻል እየተደረገ ባለው ጥረት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ ዐሻራ ከተለመደው የደን ልማት በተለየ መልኩ የግብርና ደንን (Agro-forestry) በማስፋፋት የአርሶ አደሩንና የከተማውን ማህበረሰብ የምግብ ፍላጎት በቀጥታ መመለስ ላይም ያተኮረ ነው። እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን፣ ቡና እና ሙዝ ያሉ የምግብና የፍራፍሬ ችግኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ ተተክለዋል። ይህ አካሄድ አርሶ አደሮች ከሰብል ምርት በተጨማሪ ከተተከሉት ዛፎች የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። ከዛም ባለፈ ለገበያ በማቅረብ የሚገኘው ተጨማሪ ገቢም የአርሶ አደሩን አቅም አሳድጎታል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮ አካባቢ ምህዳርን ለመጠበቅ የሚያስችሉ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል። የተተከሉት ችግኞችም ትርጉም ያላቸው የዜጎችን ተጠቃሚነትና የአካባቢ ጥበቃን ታሳቢ ያደረጉ ናቸው። ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚሆነው የጥምር እርሻ ደን ሲሆን 35 በመቶ የሚሆነው ደግሞ የደን ዛፍ ነው። ቀሪው ደግሞ የከተማ ውበት ዛፎች ናቸው። የተተከሉ ዛፎች አፈርን ከውሃ መሸርሸር በመጠበቅና የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጨምር በማድረግ የሰብል ምርታማነትን ያሳድጋሉ፤ እንዲሁም የደረቁ ምንጮችን በማነቃቃት የመስኖ ልማትን ያበረታታሉ። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተከላው ሂደት፣ የንብ እርባታንና የእንስሳት መኖ አቅርቦትን በማሳደግ የዘላቂ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል። በሌላ በኩል፣ ይህ አገራዊ ንቅናቄ በከተማ ግብርና ላይ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በከተሞች ዙሪያ የሚለሙ የፍራፍሬ ችግኞች በአነስተኛ ይዞታዎች ላይ የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ናቸው። ይህ አካሄድ በከተሞች የሚታየውን የምግብ ፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን በመቅረፍ፣ በምግብ ራስን ከመቻል አንጻር የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የሚያደርግ ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገሪቱን የምግብ ዋስትና በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት እና በምግብ ራስን የመቻል አገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚተገበር ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ነው። ንቅናቄው ከተራቆቱ መሬቶች መልሶ ማገገም ባለፈ፣ በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት የሚያፋጥንበትን ሁለንተናዊ አቅም ፈጥሯል። ኢትዮጵያዊያን እንደ አድዋ እና እንደ ህዳሴ ግድብ ሁሉ በአንድ ድምጽ በመደመር እሳቤ በአንድነት ተነስተው በጋራ እየፈጸሙት ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከችግኝ መትከልም በላይ ነው። ይሄ አንድነት ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ የተላቀቀች ለቀጣናው ለአህጉሩና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በአርዓያነት እያስጠቀሳት የሚገኝ ነው። ትውልዱ በየዓመቱ በሚከናወነው በዚህ መርሃ-ግብር ዐሻራውን ከማሳረፍ ባለፈ በእንክብካቤውም የተናበበ ሆኖ መቀጠል የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን የማድረግ መሻቱን ማሳካት ይጠበቅበታል።
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያስተናግዳሉ
Aug 13, 2026 159
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያስተናግዱ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ በስፋት ያስተናግዳሉ። በደቡብ ምዕራብ፤ ምዕራብ፤ ሰሜን ምዕራብ፤ ሰሜን፤ መካከለኛው፤ ምሥራቅ እና ሰሜን ምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚኖራቸው በመግለጫው ተመላክቷል። በምዕራብ፤ ሰሜን ምዕራብ ፤ ደቡብ ምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች እርጥበታማ የአየር ሁኔታም ከመጠናከሩ ጋር በተገናኘ በተጠቀሱት አካባቢዎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያስተናግዱ ይጠበቃል። በሰሜን ምሥራቅ፤ ምሥራቅ እና ደቡብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ደግሞ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል። በተመሳሳይ ሁኔታ በሰሜን ምዕራብ፤ ደቡብ ምዕራብ፤ መካከለኛው፤ ምዕራብ እና ሰሜን ምሥራቅ የሀገሪቱን አካባቢዎች ላይ አልፎ አልፎ ከሚከሰቱት የአየር ሁኔታ ክስተቶች ጋር ተያይዞ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል። ኢንስቲትዩቱ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ፤ የመኸር ሰብል አብቃይ፤ አርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረውን እርጥበት ለግብርና ስራዎቻቸው ውጤታማነት በአግባቡ እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርቧል። በዚህም መሰረት የአጭር ጊዜ የመኸር ሰብሎችን በመዝራት ፣የሰብል በሽታንና አረምን አስቀድሞ በመከላከል ፣ተዳፋታማ ማሳዎች ላይ የተዘጉ የማፋሰሻና የማንጣፈፊያ ቦዮችን በማስተካከል የእርጥበት ሁኔታዎን ወደ ውጤት ሊያውሉ እንደሚገባ አመላክቷል። በተጨማሪም እርጥበት አጠር አካባቢዎች የዝናብ ውሀን ማሰባሰብና ማጠራቀም፣ የመሬት መንሸራተትና የአፈር መሸርሸር መከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን፤ የማዳበሪያ አጠቃቀምን በትክክለኛው ሰዓት ጠቀም ተገቢ መሆኑንም ገልጿል። ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው እርጥበት የሚያስተናግዱ አካባቢዎችም የሚገኘውን እርጥበት ለእርሻ በቂ መሆኑን በማረጋገጥ የአጭር ጊዜ የመኸር ሰብሎችን መዝራት ፣የአፈር ውስጥ የትነት መጠንን ለመቀነስ የሚያስችሉ አሰራሮችን መዘርጋት እና ለእንስሳት የግጦሽ ሳርን በአግባቡ መጠበቅና ማዘጋጀት ሊወሰዱአቸው ከሚገቡ ጥንቃቄዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸው ተጠቁሟል። በመሆኑም የሚመለከታቸው አካላቶች የእርጥበት ሁኔታው በውሀ አካላት ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ በመገንዘብ የጎርፍ አደጋ የመሬት መንሸራተት እንዲሁም የደራሽ ወንዝ ሙላት እና ሌሎች ተያያዥ የሆኑ የተፈጥሮ አደጋዎችን መከላከል የሚስችሉ ተግባራትን እንዲያከናውኑ ምክረ ሀሳብ አቅርቧል።      
ዩኒቨርሲቲው በብዝሃ ህይወት እና ዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ረገድ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች በምርምር እንዲፈቱ እያገዘ ነው
Aug 11, 2026 368
ሮቤ፤ ነሐሴ 5/2018(ኢዜአ)፡- የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በብዝሃ ህይወት እና ዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃና እንክብካቤ ረገድ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች በምርምር ተለይተው እንዲፈቱ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ከኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት የጎባ ቅርንጫፍ ጋር በመቀናጀት "ተስፋን እንትከል'' በሚል መሪ ሀሳብ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ዛሬ አካሄደዋል።   የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬት በየጊዜው ከሚያደርገው ተሳትፎ በተጓዳኝ በዘላቂ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ረገድ ሳይንሳዊ ምርምር እያካሄደ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው በተለይም በባሌ አካባቢ የሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን በሳይንሳዊ ምርምር የማገዝ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጾዋል። በዩኒቨርሲቲው የሚካሄዱት ምርምሮች፣ ከችግኝ ተከላ ጋር ተያይዘው በአየር ንብረትና በአካባቢ ላይ የሚደርሱ ችግሮችን በጥናት ለመለየትና መፍትሔ ለመስጠት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።   በኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት የጎባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በንቲ ኦፍገሃ በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከዩኒቨርሲቲው ጋር በተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ዙሪያ ባለፉት ሦስት ዓመታት የተሰሩት ሥራዎች የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ገልጸው፤ በተለይም የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ በመደረጋቸው ጠፍተው የነበሩ የዱር እንስሳትና ምንጮች እየጎለበቱ መምጣታቸውን ጠቁመዋል።   በችግኝ ተከላው ከተሳተፉ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት መካከል መምህር ኡመር መሐመድኑር፣ በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ እንደ ዜጋ በየዓመቱ ከመሳተፍ ባሻገር ችግኞቹ ፀድቀው ለውጤት እንዲበቁም የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ሥራው የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ለኢኮኖሚ ዕድገት መፍትሄ በሚሆን አግባብ መከናወን እንደሚገባውም እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በጎባ ክፍለ ከተማ ''ስራክ ጥብቅ ደን'' አካባቢ በተካሄደው መርሐ ግብር የደን፣ የመጠለያ፣ የእንስሳት መኖና ሌሎች ችግኞች መተከላቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 655
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 644
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 922
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1428
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር!
Aug 9, 2026 658
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር! በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን ) የገጠሩ ማህበረሰብ የጨለማ ኑሮ የተፈረደበት ይመስል ኑሮውን ማሻሻል ሳይችል እልፍ ዓመታት ተቆጥረዋል፤ ለዘመናት መብራትና ውኃ ለማግኘትና ከቴክኖሎጂ ጋር ተቀራርቦ ለመኖር ወደ ከተማ መሰደድ ብቸኛው አማራጭም ነበር። የከተሜው ዋልታ የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት የሚወሰንበት የአራሹ ገበሬ የኑሮ ደረጃ ባህላዊውን የአኗኗር ዘዬ ባለመልቀቁ ደስተኛ ጊዜ የሚያሳልፍበት ሂደት አድካሚ እንደሚሆን ግልጽ ነው። የገጠሬው የተበታተነ የአኗኗር ሥርዓትም ለገጠሬው አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፤ የእዚህን የህብረተሰብ ክፍል ምርቱን እንጂ ኑሮውን የጠየቀ አልነበረም ቢባል ግነት አይሆንም።   ቀደም ሲል በነበሩ መንግስታት ከተማን እንጂ ገጠርን ማዘመን የሚያስብ ስለመኖሩ ያጠራጥራል፤ ይህም በሀገሪቱ ለኢፍትሐዊ ዕድገት የራሱን ተጽዕኖ ሲያሳደር ቆይቷል። የመደመር መንግሥት ግን ይህን ቀይሮታል። ሀገር የመምራት ኃላፊነት ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ በከተማና በገጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ በዜጎች የኑሮ ሥርዓት ላይ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርጎ እየሰራ ነው ከተሜነት ብቻውን አድጎ የገጠሩ ማኅበረሰብ በቀድሞ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሆነ የተሟላ ዕድገት ማምጣት አይቻልም የሚል ጽኑ እምነት አለው። በእዚህም ከተማና ገጠርን ለማቀራረብ በገጠር ትራንስፎርሜሽንን የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ቀርጾ መተግበር ከጀመረ ከራርሟል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን አንዱ አካል የሆነው የገጠር ሞዴል መንደር በአርሶ አደሮች ዘንድ የሚጨበጥ ተስፋን ይዘው ከመጡ ኢኒሼቲቮች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። ከተስፋ ተሻግረው በዚህ ሞዴል መንደር የነዋሪነት ዕድልን ያገኙት ደግሞ ብርሃን አይተዋል፤ የትናት አኗኗራቸውን የቀየረ አዲስ ዛሬን በእጃቸው አድርገዋል፤ ነገን አልቀው መመልከት የግብርና ተግባራቸው አንዱ አካል ሆኗል። በአዲሱ መንደራቸው ዛሬ የሚያፈስ ቤት የለም፣ የእንስሳት ቆሻሻ ሽታ በአፍንጫቸው አይገባም፣ በሚቆረቁር እንጨት ወይም መደብ ላይ አይቀመጡም፤ የከተሜው መዘነጫ ሶፋ በሳሎናቸው ተከስቷል። ጓሮዎቻቸው ሁሉ ሙሉ እንደሆኑ አፍ አውጥተው የሚያወሩ ናቸው። በዚህ ቆስጣ፤ በዛ በኩል ጎመንና ቀይስር፤ ዘውር ሲሉ ደግሞ ከአስር የሚልቁ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፤ በአንድ ክፍል ደግሞ እናት ላም ከጥጃዋ ጋራ፣ የእንቁላል ዶሮ ከሥጋ ዶሮ ጋር ሁሉንም በአንድ ጊቢ ውስጥ ያገኛሉ። ምን ይሄ ብቻ አቮካዶ እና ፓፓያ፣ ሙዝና እንሰት፣ በርበሬና ሽንኩርት ሳይቀር ለተትረፈረፈ የአርሶ አደር ማዕድና ገበያ ራሳቸውን አዘጋጅተዋል።   አርሶ አደር ኃይሉ ሞትንሞስ በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ ናቸው። እርሳቸው "መንግስት ጨለማችንን ገፎ ብርሃን አሳየን" ሲሉ በጠንካራ ቃላት የገጠር ሞዴል መንደር ፕሮጀክት ያመጣላቸውን በጎ ነገር ይገልጻሉ። እውነት ነው ያላዩትን ብዙ ነገር አሳይቷቸዋል። ያም ብርሃን ቤት ውስጥ የሚበራ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው፣ በነገ ተስፋቸውና በኢኮኖሚያቸው ላይ የፈነጠቀ ብርሃን ነው። ዛሬ ያሉበትን ህይወትም "ለእኔ አዲስ ነገር ነው። አይቼው አላውቅም፤ መቼም በራሴ ሀሳብ አላደርገውም ነበር።" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግስት አበራልኝ ያልኩት በእጄ ያለኝን ያላየሁትን ዕድል ስላሳየኝ ነው በማለትም ሀሳባቸውን ይቀጥላሉ። እኛ ሀብት አለን፤ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም። ይልቁንም የምናባክነው ይበዛል በማለትም የቀደመ ሕይወታቸውን እያሰቡ ይቆጫሉ። አሁን ግን ብዙ ተገነዘብኩ የሚያስብል የመደመር መንግስት በመኖሩ አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። እርግጥ ነው የገጠር ሞዴል መንደር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ነው። ለአብነትም የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ማንሳት ይቻላል። የተሠሩ ሞዴል መንደሮች በመጀመሪያ የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ የመሆን ዕድል ገጥሟቸዋል። በመቀጠል ንጽሕናው ያልተረጋገጠ የመጠጥ ውኃ ወንዝ ወርዶ ከመቅዳት ተቆጥበው በመንደራቸው የተገነባውን የከረሰ ምንድር ውሃ ከቧንቧ ቀድተው መጠጣት አስችሏቸዋል። በእሳት እና ኩራዝ ጭስ ሲሰቃዩ የነበሩ ዓይኖቻቸው ዛሬ ከሶላር ቴክኖሎጂ የመነጨ ብርሃን ማየት ጀምረዋል። ብርሃን ብቻ አይደለም ለወትሮ ለገበያ ወደ ከተማ ብቻ ሲወጡ ይመለከቱ የነበረውን ቴሌቪዥን ዛሬ በቤታቸው አስገብተው የመረጃና የመዝናኛ ዓለምን ተቀላቅለዋል። አርሶ አደሮቹ ቴሌቭዥንን ከመዝናኛነት ይበልጥ ለመረጃ እንደሚጠቀሙት ያነሳሉ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በዜና ተከታትሎ መረዳት፣ የገበያ ሁኔታን ማወቅ፣ የግብርና ሥራ ተሞክሮን መቅሰምና የአየር ንብረት ሁኔታን ጨምሮ ለሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙት ከቴሎቪዥን መስኮት እንደሆነ ይናገራሉ።   በጓሯቸው የተትረፈረፈ የሌማት ትሩፋት ምርት መሰብሰብ የሚያስችላቸው ምቹ ሁኔታ ደግሞ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው። በተለይ መንግስት በጓሯቸው ጥምር እርሻ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የነገ ኢኮኖሚያቸውን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ ነው። ከተማን መናፈቅን ያስቀረው የገጠር ሞዴል መንደር ያኔ ከጅምሩ አመኔታን አላገኘም። የቦታና የአካባቢ ቁሳቁስ ለማቅረብ ዝግጁ እስካለመሆን የደረሱ አርሶ አደሮችም ነበሩ። በወቅቱ ጉዳዩን እንደፌዝ አዩት። ዛሬ ግን ውጤቱን በአግራሞት በዐይናቸው ተመለከቱ። የተናገረውን የሚከውን፤ የጀመረውን የሚጨርስ የመደመር መንግሥትን ተጨባጭ ስራዎች በማረጋገጥ እንደ ትንግርት ቆጠሩ። ዛሬ በየአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በቁጭት ተሞልተው መንደራቸውን ወደዚህ የሞዴል መንደር እሳቤ ለመቀየር ተነሳስተዋል። የጌሊት ቀበሌ አርሶ አደሮቹ መኮንን አርዶ እና ነጻነት ተስፋሁን ለዚህ ተጠቃሾች ናቸው። ያዩትን ተሞክሮ በራስ አቅም በመንደራቸው ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ከተማ ሄደን የምናወጣውን ወጪና የምናባክነውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት እዚሁ መዝናናት የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል።   "ይህ ዕድል ለእኛ ለአርሶ አደሮች በታሪክ የሚነገር ትልቅ አጋጣሚ ነውም" ይላሉ። በጤዛ እየራስን እንጓዝበት የነበረው መንገዳችን ዛሬ ሰፍቷል። ተሽከርካሪ በደጃችን ስለሚያልፍም ምቹ ዕድልን ይዞልን መጥቷል። ይህን ጅምር ተግባር ወደ ላቀ ውጤት ማሸጋገር የእኛ ድርሻ ነውና ጠንክረን እንሠራለንም ብለዋል።   ይህን ዕድል ወደ ትልቅ አቅም ለመቀየር መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ የሸሸቃ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር አልዓዛር ዘርክናንስ ናቸው። የዶሮና የከበት እርባታን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ ሥራን ከመደበኛው የእርሻ ሥራ ጋር አስተሳስረው በመሥራት ከቤተሰብ ፍጆታ ተርፎ ለገበያ የሚበቃ ምርት ለማምረት እየተዘጋጁ ነው።   ይህም የገቢ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ልጆቻቸው ወተትና የወተት ተዋጽኦ በቤታቸው እንዲያገኙ ያደርጋል። ማር፣ እንቁላል እና ሥጋ እንዳያምራቸው የሚያደርግ ትልቅ ኢኒሼቲቭም ነው። አንዱ ቢጎድል በሌላው እየሞሉ የሚኖሩበትን የሥራ መስክ አጠናክረው ለውጤት አብቅተው ለተሻለ ለውጥ እንደሚሠሩ አክለዋል። የአርሶ አደር እናቶች ዘምቢል ይዘው አትክልትና ፍራፍሬ ሸመታ ወደ ገበያ ማቅናት የለባቸውም። ይልቁንም ከጎሮቸው ወደ ገበያ ይዞ መውጣት የኑሮ ዘዬያቸው ወግ ነው። ወይዘሮ መሠረት ማሞ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ያልለመዱትን አዲስ ሕይወት ከአዲስ ተስፋ ጋር መጀመራቸውን ከሚናገሩት መካከል ናቸው።   ትናንት ኩሽናቸው፣ መኝታቸው እንዲሁም የከብትና የዶሮ ማደሪያ በአንድ ቤት ወስጥ የተወሰነ እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን ሽንት ቤትና መታጠቢያ ቤት ሳይቀር ለየብቻ የራሱ የሆነ ቤት ተገንብቶ ጽዳቱ የተጠበቀ ኑሮ መኖር ጀምረዋል። ቤታቸው ሲገቡና ሲወጡ ለዓይን ማራኪ፤ ለመቀመጥ ምቹ፤ ለመተኛትም ንጹህና ወገብ የሚያሳርፍ ሆኖ አግኝተዋል። እናም በዚህ እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። "መንግስት እንደ አባት ጎዶሏችንን ሞልቷል" ሲሉም ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ የአርሶ አደሮችን ሕይወት ብሩህ ያደረገው የገጠር ሞዴል መንደር ኢኒሼቲቭ በመላው ሀገሪቱ በመስፋፋት ላይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 16 ሞዴል መንደሮች በ16 ወረዳዎች ተገንብተዋል።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ኢኒሺዬቲቩ የአርሶ አደር ኑሮ ዘዬን ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ጋር ለማቆራኘት ያስቻለ ነው። የተሻለ መኖሪያ ቤት ኖሮት በጓሮው የሚበላ ነገር ካጣ ሕይወቱ ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም። ይህም በመሆኑ ቤቶቹን ከእያንዳንዱ የግብርና ልማት ዘርፎች ጋር በማጣመር እንዲገነቡ የተደረገው። ይህም የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ስትራቴጂን የሚያጠናክርና ገበያን የማረጋጋት ዓላማን የያዘ ጭምር ነው። በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ የተገኘው መልካም ውጤት በቀጣይ በሁሉም ወረዳዎች የሚስፋፋ ሲሆን በዞን እና ወረዳ መዋቅሮች ድጋፍና ክትትል በቀበሌ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አንስተዋል። ይህ ኢኒሼቲቭ የሀገራዊ ብልጽግና ጉዞ አንዱ አቅም ነው። የተደመረ የማኅበረሰብ ብልጽግና ሀገርን ከፍ ያለ የዕድገት ማማ ላይ ያስቀምጣታል። እነሆ የክልሉ አርሶ አደሮች የአካባቢያቸውን ጸጋ ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ የሚቀይሩበት መስክ በሞዴል መንደር ምክንያት እጃቸው ላይ ደርሷል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉትም በብዙ መንገድ ጨለማ የከበበው የገጠሩ ማኅበረሰብ ሕይወት ዛሬ ብርሃን ማየት ጀምሯል። ይህ የብርሃን ፋና እየተቀጣጠለ ወደ ብዙኃኑ ሊደርስ የሁሉንም ፍላጎት አነሳስቷል። ሥሩ ከማለት ይልቅ ሠርቶ ማሳየትን የሚያስቀድመው የመደመር መንግስት የፈጠራቸው የገጠር ሞዴል መንደሮች ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን በዘላቂነት የሚያሳምሩ ናቸው። ሰላም እንሰንብት!  
ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የአፍሪካ ኃያል ሀገር እየሆነች ነው-ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት
Aug 7, 2026 575
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት የመጪው ዘመን የአፍሪካ ኃያል ሀገር ወደመሆን እየተሸጋገረች ነው ሲል ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት ዘግቧል። ፈርስት ፖስት ሚዲያ ኢትዮጵያን በተመለከተ በሠራው ትንታኔው የሰው ዘር መገኛ፣የጥንታዊ መንግስታት ምድር፣የንግድ መስመሮች እና ከፍ ያለ የአፍሪካ ታሪካዊ መሰረት ያላት ሀገር መሆኗን አውስቷል። ሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ከቀድሞ ገናና ታሪኳ እኩል ታላቅ የሆነ አዲስ ምዕራፍ ለመገንባት በትጋት ላይ መሆኗን አንስቷል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት በቀጣናው እና የአፍሪካ ኃያል ሀገር መሆን የሚያስችላትን እንዲሁም የአህጉሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚበይንና የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሠራች መሆኗንም እንዲሁ። ለረጅም ዓመታት ዓለም ኢትዮጵያን የሚያውቃት በጦርነት፣በድርቅ እና በፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንደነበር በማስታወስ፥ዛሬ ግን ሀገሪቱ ይህንን የተዛባ ትርክት በኢነርጂ መሠረተ ልማት፣ በአቪየሽን፣ በማዕድን እና በዲጂታል ኢኮኖሚ አስደማሚ ለውጦች ለመቀየር እየሠራች ነው ብሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ተሻግራ እንዴት በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት ካላቸው ኢኮኖሚዎች ቀዳሚዋ ሆና ልትቀጥል ቻለች? የሚለውን ጥያቄ በማንሳትም በዝርዝር መልሶቹን ያብራራል። የዚህ ዋና ጥያቄ ዝርዝር ምላሽ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት እየተተገበሩ የሚገኙ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ ነው ያለው ሲል አንስቷል።   • የመጀመሪያው የኢነርጂ አብዮት እና ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ነው። በዚህ የኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ጎልቶ የሚነሳው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሲሆን፣ ከ5 ሺህ ሜጋዋት በላይ የማመንጨት አቅም ያለው የአፍሪካ ትልቁ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት መሆኑን ፈርስት ፖስት በዘገባው ጠቅሷል። ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መሻቶች መሰረት፣የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የውጭ ምንዛሬ እና የቀጣናዊ ተጽዕኖ መፍጠሪያ አቅም መሆኑንም አብራርቷል። የሕዳሴ ግድብ ልዩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ከዓለም ባንክ ወይም ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አንድ ሳንቲም ሳይበደር በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም፣ ላብና ገንዘብ የተገነባ አፍሪካውያን በራሳቸው ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየነው ብሏል። ለኢትዮጵያውያን ግድቡ ከኮንክሪት እና ከተርባይን በላይ ትርጉም አለው ያለው ይህ የፈርስት ፖስት ዘገባ፥ እጅግ የላቀ እራስን የመቻል እና የኢኮኖሚ ነፃነት ማሳያ ሐውልት መሆኑንም ተንትኗል። ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን ለኬንያ፣ ለጂቡቲ እና ለሱዳን በመሸጥ ኤሌክትሪክን ወደ ከፍተኛ ገቢ ማመንጫነት እየቀየረች ከመሆኑም በላይ የመላው ምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የትስስር ማዕከል ሆናለች ነው ያለው። • የኢትዮጵያ የዕድገት ምሰሶ አቪዬሽን እና ቀጣናዊ ትስስር ኢነርጂ ብቻውን ኢኮኖሚያዊ አቅምን አይገነባም፤ ይልቁንም ኢነርጂ ኢንዱስትሪን ያነቃቃል፣ ትስስር ዓለም አቀፍ ንግድን ይመግባል ያለው ፈርስት ፖስት፥የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን ለላቀ የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ጉዞ መጀመሩን አንስቷል። በ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በየዓመቱ እስከ 110 ሚሊዮን ተጓዦችን እና ወደ 4 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ የዕቃ ጭነት ማስተናገድ አቅም አለው። ሙሉ በሙሉ ግንባታው ሲጠናቀቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከታላላቅ የአቪዬሽን ማዕከላት አንዱ ይሆናል ብሏል።   ይህ ፕሮጀክት የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ መናኸሪያ የሆነችውን አዲስ አበባንና አፍሪካን፣ከሌሎች የዓለም ክፍሎች የሚያስተሳስር ዋና የመተላለፊያ ማዕከል እንደሚሆንም ተገልጿል። ስለዚህ አዲሱ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንት እና ለቱሪዝም፣ ለዓለም የዲፕሎሲ ትብብር ጉልህ ሚና እንዲያበረክት ታስቦ እየተገነባ ነው ብሏል። • የማዕድን ኢንቨስትመንትና በምግብ ራስን መቻል በሌላ በኩል ከኢትዮጵያ መሬት በታች ላለው የማዕድን ሀብቷ ትኩረት በመስጠት የልማት አብዮት እያካሄደች ስለመሆኑም ተንትኗል። ሀገሪቱ የወርቅና ሌሎች ማዕድናት ማውጫ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት አዳዲስ የውጭ ምንዛሬ ምንጮችን እያፈራች የማዕድን ኢንዱስትሪዋን እያሳደገች ነው። ወርቅ በፍጥነት ከኢትዮጵያ ቀዳሚ የወጪ ንግድ ምርቶች አንዱ በመሆን ለረጅም ጊዜ በግብርና ላይ ብቻ ጥገኛ ሆኖ የቆየውን ኢኮኖሚ ወደ ብዝኃ ዘርፍ እያሸጋገረ ይገኛል። በሌላ በኩል በምግብ ራስን ከመቻል ውጭ የትኛውም ኢኮኖሚያዊ ለውጥ የተሟላ ሊሆን አይችልም ያለው የፈረስት ፖስት ዘገባ፥ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆኑን ጠቅሷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን እንድትችል በጀመረው የለውጥ ጉዞ አስደማሚ ውጤት እያመጣ ነው ብሏል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከጉባ ብስራቶች አንዱ የሆነውና በሶማሌ ክልል እየተገነባ የሚገኘው የማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት በየዓመቱ 3 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ዩሪያ ማዳበሪያ ማምረት የሚችል ነው። ይህም ከውጭ የሚገባውን ማዳበሪያ ጥገኝነት በመቀነስ የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚያስችል አብራርቷል። "የምግብ ዋስትና የእኛ ስትራቴጂካዊ ጣልቃ ገብነት ነው።ያንን ግብ እውን ለማድረግ ግብአቶች ላይ መስራት አለብን።በግብአት ላይ መስራት ካልተቻለ የምግብ ዋስትናን እውን ለማድረግ መንገድ የለውም" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ በማካተት ዘገባው ሰፊ ሽፋን ሰጥቷል። ዲጂታላይዜሽን እና የኢንቨትመንትና የገበያ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ለውጥ ወደ ዲጂታልም እየተሸጋገረ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እንደተናገሩት የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠና ከዕቅዱ ቀድም ከመሳካቱም በላይ በርካታ ወጣቶች የዲጂታል እውቀት ባለቤት አድርጓል።   በተመሳሳይ የዲጂታል ትስስር እየሰፋ ሲሆን የ4ጂ እና 5ጂ አገልግሎቶች በበርካታ ከተሞች ተደራሽ ሆኗል። ኢትዮጵያ ለበርካታ አስርት ዓመታት ተዘግተው የቆዩ እንደ ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ባንክ እና የካፒታል ገበያዎች ያሉ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጓንም አድንቋል። የካፒታል ገበያን መጀመሯም የግል ካፒታል ልውውጥን በማጎልበት ለኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተንትኗል። እነዚህ ማሻሻያዎች በአጠቃላይ በመንግስት ቁጥጥር ስር ከነበረው የኢኮኖሚ ወደ ግል ዘርፍ ኢንቨስትመንት እያደገ የሚሄድ ኢኮኖሚ መሰረታዊ ለውጥን እየተገነባ መሆኑን ያሳያሉ ነው ያለው። ኢትዮጵያ ካላት የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ አኳያ እድልና ፈተናዎች ከፊቷ መሆናቸውን በማንሳት፥ አዲሱን የዓለም አቀፍ የትብብር ጥምረት ብሪክስ አባል መሆኗን አውስቷል። ከቻይና፣ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት፣ ከምዕራባውያን አጋሮችና ከአፍሪካ ኢንቨስተሮች ኢንቨስትመንትን እየሳበች እንደምትገኝም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ጎራ ሳትለይ ከሁሉም የዓለም ሀገራት ጋር ትብብሯን እያጠናከረች ነው ብሏል። ዓለም ኢትዮጵያን የምታስታውሰው በጦርነት ቢሆንም፥ኢትዮጵያ ዓለም በአዲሱ የለውጥና የስኬት ጉዞዋ እንዲያስታውሳት እየሠራች ነው። ለዚህም በመላው ሀገሪቱ በሁሉም ዘርፍ ግዙፍ የኢኮኖሚ ሽግግር እየተካሄደ ሲሆን፥ ይህ የኢትዮጵያ ጉዞ ለቀጣዮቹ ዓመታት የቀጣናውንና የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊና አጠቃላይ ገጽታ በአዲስ መልኩ የሚቀርጽ ነው ሲል ፈርስት ፖስት ዘገባውን አብራርቷል።
ያቀደችውን በተግባር የምታሳካ ታላቅ ሀገር
Aug 3, 2026 883
የአንድ ሀገር ታላቅነት ከሚለካባቸው ጉዳዮች አንዱ የተያዙ ሀገራዊ እቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም ዋነኛው ነው። ኢትዮጵያም በዛሬው እለት በአንድ ጀምበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አዲስ ታሪካዊ ስኬት፣ ሀገሪቱ ያቀደችውን በተግባር ማሳየት የምትችልና ትልልቅ ህልሞችን የመተርጎም አቅም ያላት ታላቅ ሀገር መሆኗን ለመላው ዓለም በተግባር ያስመሰከረ ነው። ይህ በአንድ ጀምበር የተከናወነ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በርካታ ጥልቅ ትርጉሞችን የያዘ ነው፡ በአንድ ጀንበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ግዙፍ የሎጂስቲክስ፣ የዝግጅትና የህዝብ ንቅናቄ ስራን ይጠይቃል።   ይህ ስኬት ሀገሪቱ ማንኛውንም ታላቅ አገራዊ እቅድ አቅዳ እስከ መጨረሻው የትግበራ ምዕራፍ ድረስ በብቃት የመምራትና የማስተባበር ተቋማዊና ህዝባዊ አቅም እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ዕድሜ፣ ጾታ፣ ወይም ልዩነት ሳይለያያቸው በአንድ ቀን ለተመሳሳይ አገራዊ ዓላማ መቆማቸው፣ ኢትዮጵያውያን ለጋራ እድገታቸውና ለሀገራቸው የወደፊት ተስፋ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትና አንድነት አሳይቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት ዋና ስጋት በሆነበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ እርምጃ ለችግሩ መፍትሔ በመስጠት ረገድ የዓለም አቀፍ መሪነቷን ያስመሰከረችበት አጋጣሚም ጭምር ነው። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የገጠሟትን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፈተናዎች ተሻግራ፣ አቅሟን አስተባብራ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ለዜጎቿም ሆነ ለውጭው ዓለም የሰጠችው ትልቅ የራስ መተማመንና የተስፋ መልእክት ነው። በአጠቃላይ፣ በአንድ ጀምበር የተከናወነው ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ አርቆ የማሰብና የማቀድ ችሎታዋን ብቻ ሳይሆን፣ ያቀደችውንም በአንድነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት በማውረድ በተግባር የምታሳይ ታላቅ ሀገር መሆኗን በግልጽ ያረጋገጠ አኩሪ ተግባር ነው።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ ትንሳኤ ብስራት!!
Aug 2, 2026 690
በሐዊ አጫሉ መግቢያ፡- የኢንዱስትሪ ዘርፍ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬን ከሚወስኑ ዋነኛ የብልፅግና ማረጋገጫ ምሰሶዎች መካከል በግምባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ዘርፉ ምርትን ከማሳደግ ባሻገር የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የሀገር ውስጥ ምርታማነትን የሚያፋጥን የልማት ሞተር ነው። ኢትዮጵያም ከግብርና መሠረት የተነሳ ኢኮኖሚዋን ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ሁሉን አቀፍ የምርት ሥርዓት ለማሸጋገር ከምታደርገው ጥረት መካከል ኢንዱስትሪውን በቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶነት በማካተት እየሰራችበት ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ አምስት ዐበይት የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት ምሰሶዎች ተመሥርቶ እየተመራ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥ ኢንዱስትሪው የምርት አቅምን በማሳደግ የግብርና ምርቶችን ወደ ተጨማሪ እሴት በመቀየርና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ እያስገኘ ነው። ይህንን ሽግግር እውን ለማድረግ የምርት አቅምን ማሳደግ፣ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር፣ የአቅርቦት ሰንሰለትን ማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና የሰው ኃይል ልማት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ የቀድሞ ገጽታ፤ ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ለውጥ መንገድ!! በቀደሙት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለያዩ ዕድሎችንና ፈተናዎችን በማስተናገድ በርካታ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል። ሀገሪቱን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር በተደረጉ ጥረቶች የተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተገንብተዋል። እነዚህ ፓርኮችም በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የተሞከረበት ወሳኝ ምዕራፍ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ ይህ ጉዞ በበቂ መሠረተ ልማት፣ በተሟላ የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና በተቀናጀ የምርት ሰንሰለት እጥረት ምክንያት በበርካታ ፈተናዎች ለመውደቅ ተገዶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ውስንነት፣ ዕውቅትና ክህሎትን የተሰላበሰ የሰው ኃይል አለመኖር፣ የፋይናንስ እጥረት፣ ውስብስብና አስቸጋሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትና የገበያ ትስስር እጥረት የዘርፉን እድገት ገድበው የነበሩ ሁነኛ ተግዳሮቶች ናቸው። ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ምርታማነት፤ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የለውጥ ፍኖት!! ባለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ ዘርፉ የተስተዋሉ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታትና የሀገሪቱን የማምረት አቅም ለማሳደግ አዳዲስ የለውጥ አቅጣጫዎች ተነድፈው ተተግበረዋል። በተለይም ኢንዱስትሪን ከተለመደው የምርት ሥርዓት በማሻገር ወደ ተወዳዳሪ ዘመናዊና ውጤታማ የማምረቻ ማዕከል ለመቀየር የተለያዩ የፖሊሲማሻሻያዎች ተደርገዋል። የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ፣ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን፣ የሰው ኃይል አቅምን ማሳደግና የግብርና-ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር በዘርፉ የተወሰዱ ሁነኛ የለውጥ እርምጃዎች ናቸው። በዚህም የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት በማጎልበት ከሀገር ውስጥ ገበያ እስከ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ድረስ ውጤት እያስገኘ ነው። የግል ባለሃብቱ ሚና፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሞተር!! የኢንዱስትሪ ልማት በመንግሥት ጥረት ብቻ የሚሳካ አይደለም። የግል ዘርፉ በካፒታል፣ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂና በአስተዳደር ብቃት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ለዘርፉ ዕድገት የማይተካ ሚና አለው። በዚህ ረገድ የግል ባለሃብቱ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዋና አጋር እንዲሆን የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተሻሽለው እየተሰራባቸው ይገኛል። ይህም የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት በማሻሻል፣ የንግድ ሥራ ሂደቶችን በማቀላጠፍ፣ የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋትና የምርት አቅምን በማሳደግ የግሉን ዘርፉ የምርታማነት አቅም እያጎለበተ ነው። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትንሳኤ ብስራት!! በሀገራችን የኢኮኖሚ አቅጣጫ ውስጥ የምርትና አገልግሎት አሰጣጥን በማቀናጀት አዲስ ምዕራፍ ከከፈቱ ዐበይት ሀገራዊ መርሃ-ግብሮች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተጠቃሽ ነው። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማምረት ባህልን በማሳደግ ዘርፉ ወደ አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚሸጋገርበት ሁነኛ ዕድልን ፈጥሯል። ንቅናቄው የማምረት አቅምን በማሳደግ ሥራ ያቆሙ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ መመለስ፣ የአምራቾችን ችግሮች በፍጥነት መፍታትና አዳዲስ ባለሃብቶችን ወደ ዘርፉ በመሳብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤ እያበረከተም ይገኛል። በዚህ ሂደት በፋይናንስ፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በውጭ ምንዛሬና በተቋማዊ ቅንጅት ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎች የአምራች ዘርፉን የምርታማነት አቅም በማጎልበት ጉልህ ሚና ተጫውቷል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲያንሰራራ በማድረግ የምርታማነት አብዮት እንዲቀጣጠል እያደረገ ይገኛል። የንቅናቄው ዋና ዓላማ በአምራች ዘርፉ የነበሩ ማነቆዎችን በመፍታት የኢትዮጵያን የማምረት አቅም ማሳደግ ነው። ይህም ሥራ ያቆሙ ወይም በአቅማቸው ልክ ያልሠሩ ፋብሪካዎችን ወደ ሙሉ ምርት በመመለስ የአምራቾችን ችግር በተቀናጀ መንገድ መፍታት፣ የፋይናንስና የግብዓት ተደራሽነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጓል። በዚህ ሂደት የማምረቻ ዘርፉ በአዲስ የሥራ ባህል፣ በተቋማዊ ቅንጅትና በፈጣን ውሳኔ አሰጣጥ እየተመራ መሆኑ የለውጡን ፍጥነት እያሳደገው ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ተደራሽነትን ማሻሻልና የምርት ጥራትን ማረጋገጥ የኢንዱስትሪው ትንሳኤ ዋና ማሳያዎች ናቸው። ለአብነትም፡- የፋይናንስ አቅምና የብድር አቅርቦት ማሻሻል፡- የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ እንቅፋት የሆነውን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ በተደረገው ርብርብ፣ የብድር አቅም ቀደም ሲል ከነበረበት 40 ቢሊዮን ብር ወደ 115 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ለአምራቾች ሰፊ የካፒታል አቅም መፍጠር ተችሏል። የውጭ ምንዛሬ ግኝትና የግብዓት ድጋፍ ማደግ፡- ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ይቀርብ የነበረው የውጭ ምንዛሬ መጠን አሁን ላይ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንዲደርስ ተደርጓል። ይህም ፋብሪካዎች ከአቅማቸው በታች እንዲሠሩ ያስገድድ የነበረውን የምርት ውስንነት በከፍተኛ ደረጃ አቃሎታል። የምርት ዕድገት፣ ተኪ ምርትና የኤክስፖርት አፈጻጸም፡- ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ ከነበረበት 348 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5.9 ቢሊዮን ዶላር በማደግ ግዙፍ ሀገራዊ ድል ተመዝግቧል። እንዲሁም በኤክስፖርት ገበያ የሚገኘው ገቢ ከ385 ሚሊዮን ዶላር ወደ 607 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ማለት ችሏል። ተቋማዊ ቅንጅትና አዲስ የሥራ ባህል ማዳበር፡- በክልሎችና በፌዴራል ተቋማት መካከል የነበረውን የቢሮክራሲ ጫና በመቀነስ ፈጣን ውሳኔዎች እንዲሰጡ መደረጉ፤ እንዲሁም ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርትን በኩራት የመጠቀም እና የሀገር ፍቅር ስሜትን ከአምራችነት ጋር የማስተሳሰር ትልቅ ማህበራዊ ንቃተ-ህሊና መገንባት ተችሏል። የወደፊት ተስፋ፤ ኢትዮጵያ አዲሲቷ አፍሪካዊት የኢንዱስትሪ ምርታማነት ተምሳሌት ሀገር!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ በቀጣይ ዓመታት ከተለመደው ማምረት ወደ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ሥርዓት እንዲሸጋገር ይጠበቃል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሜሽን፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና የፈጠራ ሥርዓቶችን ወደ ማምረቻ ዘርፉ ማስገባት የወደፊቱ ትኩረት ይሆናል። በተመሳሳይም ጠንካራ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስር፣ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት፣ ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአህጉራዊ ገበያ ተደራሽነት የሀገሪቱ ቀጣይ የኢንዱስትሪ ግቦች ናቸው። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) የሚፈጥረውን ሰፊ የገበያ ዕድል በመጠቀም ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችል መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ማጠቃለያ፡- ማምረት፤ የኢትዮጵያ የብልፅግና ቁልፍ መሳሪያ!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ተጨማሪ እሴት ያለው ምርት አቅራቢነት በማምራት እመርታዊ ውጤቶችን እያስገኘ ነው። የኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ማለት ፋብሪካዎችን ብቻ ማስፋፋት ሳይሆን የሀገርን ምርታማነት፣ የወጣቶችን ዕድል፣ የኢኮኖሚ ነፃነትንና የልማት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን የዛሬ ልማት ብቻ ሳይሆን የነገውን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚገነባ ሀገራዊ ራዕይ ነው።  
ትንታኔዎች
አረንጓዴ ዐሻራ፦ የምግብ ሉዓላዊነት ምሰሶ
Aug 14, 2026 93
(በሙሴ መለሰ) የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአፈር መሸርሸር እና የተፈጥሮ ሀብቶች መመናመን በአሁኑ ወቅት የዓለማችን ዋነኛ የህልውና ስጋቶች ሆነዋል። ኢትዮጵያም የዚህ ችግር ተጠቂ ናት። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ ተግዳሮቶቹን በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ነው። የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም፣ የደን ሽፋንን መጨመር፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት በወቅቱ አረንጓዴ ዐሻራ ሲጀመር የነበሩ አበይት አላማዎች ናቸው። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ መጀመሩ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘንድሮው ዓመት ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ መቀመጡን እና በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የምታስተናግደው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ድረስ የሀገሪቱን ግብ ወደ 65 ቢሊዮን ከፍ ለማድረግ መታቀዱን ገልጸዋል። ሐምሌ 27/ 2018 በተካሔደው የዘንድሮው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይም 800 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል ታቅዶ፣ 805 ነጥብ3 ሚሊዮን በመትከል ከእቅዱ በላይ ማሳካት ተችሏል። ከ26 ነጥብ2 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው የተሳተፉበት ይሄ መርሃ-ግብር በአጠቃላይ 294 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ነበር። በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ለመትከል ከታቀደው ስምንት ቢሊዮን ችግኞች መካከልም ከ6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ መተከሉን መረጃዎች ያሳያሉ። የአረንጓዴ ዐሻራ ከአካባቢ ጥበቃ ስራ ባሻገር ሀገራዊ የምግብ ዋስትናን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። መርሃ-ግብሩ ከተራቆቱ መሬቶች መልሶ ማገገም ባለፈ፣ በምግብ ራስን ለመቻል እየተደረገ ባለው ጥረት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ ዐሻራ ከተለመደው የደን ልማት በተለየ መልኩ የግብርና ደንን (Agro-forestry) በማስፋፋት የአርሶ አደሩንና የከተማውን ማህበረሰብ የምግብ ፍላጎት በቀጥታ መመለስ ላይም ያተኮረ ነው። እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን፣ ቡና እና ሙዝ ያሉ የምግብና የፍራፍሬ ችግኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ ተተክለዋል። ይህ አካሄድ አርሶ አደሮች ከሰብል ምርት በተጨማሪ ከተተከሉት ዛፎች የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። ከዛም ባለፈ ለገበያ በማቅረብ የሚገኘው ተጨማሪ ገቢም የአርሶ አደሩን አቅም አሳድጎታል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮ አካባቢ ምህዳርን ለመጠበቅ የሚያስችሉ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል። የተተከሉት ችግኞችም ትርጉም ያላቸው የዜጎችን ተጠቃሚነትና የአካባቢ ጥበቃን ታሳቢ ያደረጉ ናቸው። ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚሆነው የጥምር እርሻ ደን ሲሆን 35 በመቶ የሚሆነው ደግሞ የደን ዛፍ ነው። ቀሪው ደግሞ የከተማ ውበት ዛፎች ናቸው። የተተከሉ ዛፎች አፈርን ከውሃ መሸርሸር በመጠበቅና የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጨምር በማድረግ የሰብል ምርታማነትን ያሳድጋሉ፤ እንዲሁም የደረቁ ምንጮችን በማነቃቃት የመስኖ ልማትን ያበረታታሉ። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተከላው ሂደት፣ የንብ እርባታንና የእንስሳት መኖ አቅርቦትን በማሳደግ የዘላቂ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል። በሌላ በኩል፣ ይህ አገራዊ ንቅናቄ በከተማ ግብርና ላይ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በከተሞች ዙሪያ የሚለሙ የፍራፍሬ ችግኞች በአነስተኛ ይዞታዎች ላይ የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ናቸው። ይህ አካሄድ በከተሞች የሚታየውን የምግብ ፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን በመቅረፍ፣ በምግብ ራስን ከመቻል አንጻር የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የሚያደርግ ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገሪቱን የምግብ ዋስትና በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት እና በምግብ ራስን የመቻል አገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚተገበር ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ነው። ንቅናቄው ከተራቆቱ መሬቶች መልሶ ማገገም ባለፈ፣ በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት የሚያፋጥንበትን ሁለንተናዊ አቅም ፈጥሯል። ኢትዮጵያዊያን እንደ አድዋ እና እንደ ህዳሴ ግድብ ሁሉ በአንድ ድምጽ በመደመር እሳቤ በአንድነት ተነስተው በጋራ እየፈጸሙት ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከችግኝ መትከልም በላይ ነው። ይሄ አንድነት ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ የተላቀቀች ለቀጣናው ለአህጉሩና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በአርዓያነት እያስጠቀሳት የሚገኝ ነው። ትውልዱ በየዓመቱ በሚከናወነው በዚህ መርሃ-ግብር ዐሻራውን ከማሳረፍ ባለፈ በእንክብካቤውም የተናበበ ሆኖ መቀጠል የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን የማድረግ መሻቱን ማሳካት ይጠበቅበታል።
ከአረንጓዴ አሻራ እስከ ዓለም ገበያ - የኢትዮጵያ ቡና ልማት አዲስ የዕድገት ምዕራፍ
Aug 13, 2026 339
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቡና መገኛ ከመሆኗም ባለፈ ምርቱ አሁንም ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብትና ማህበራዊ ህይወት ትልቅ መሰረት ያለው ነው። የዓለም የቡና ዝርያዎች ሁሉ መገኛ የሆነው የአረቢካ ቡና ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘውም በኢትዮጵያ እንደሆነ ይታወቃል። በኢትዮጵያ ቡና መጠጣት የዕለት ተዕለት ባህል ሲሆን፣ የቡና አፈላል ስነ ስርዓት ሰላምን፣ አንድነትንና ማህበራዊ ውይይትን የሚያጠናክር ትልቅ እሴት ተደርጎም ይወሰዳል። በአሁኑ ወቅት ቡና ለሀገሪቱ ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኝ ቀዳሚው የግብርና ምርት በመሆን ማዕከላዊ የኢኮኖሚ ሚናውን እየተጫወተ ይገኛል። አብዛኛው የኢትዮጵያ ቡና የሚመረተው በተፈጥሯዊ መንገድ በገበሬዎች ማሳ ላይ ወይም በዱር ውስጥ በመሆኑ፣ ለሰው ሰራሽ ማዳበሪያና ኬሚካል ተጋላጭ አይደለም። ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተመራጭነት ይበልጥ ከፍ አድርጎታል። ከኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ምሰሶ አንዱ የሆነው ቡናችን ለሀገሪቷ እያስገኘ ያለው ገቢም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ካነሷቸው ጉዳዮች መካከልም አንዱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዋልታ የሆነው ቡና ነበር። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከብራዚልና ኮሎምቢያ በመቀጠል በዓለም 3ኛዋ ትልቋ የቡና ላኪ ሀገር መሆኗን እና በአፍሪካም ቀዳሚ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጸዋል። በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ከቡና ወጪ ንግድ 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን፣ ይህ ውጤት ባለፉት 17 ዓመታት በድምሩ ከተገኘው 3 ነጥብ3 ቢሊዮን ዶላር ጋር ሲነጻጸር በዘርፉ የተመዘገበውን ከፍተኛ ዕድገት ያሳያል ብለዋል። ለተመዘገበው ውጤት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም አጠናክራ መጠቀም እንዳለባት ተናግረዋል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ የኢትዮጵያን የቡና ዘርፍ ከዘልማዳዊ አሰራር ወደ ዘመናዊ ምርታማነት ለማሸጋገር የሚያስችል አዲስ የ10 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ እና የተሻሻለ የልማት ፓኬጅ መዘጋጀቱን በቅርቡ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል። ቡና በሀገሪቱ ኢኮኖሚ፣ የሚሊዮን አርሶ አደሮች የኑሮ መሠረትና የወጪ ንግድ ዋነኛ ምሰሶ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ታላቅ ሀብት በጥራትና በዘላቂነት በማሳደግ ከምርት ወደ እሴት፣ ከእሴት ወደ ዓለም ገበያ ማሸጋገር የዘርፉ ዋነኛ አቅጣጫ መሆኑን ተናግረዋል። ይህንኑ ስትራቴጂ ለማሳካት የተጀመረው ሃገራዊ የቡና ምርትና ምርታማነት ኢኒሼቲቭ በአሁኑ ወቅት በሔክታር 9 ኩንታል የሆነውን የቡና ምርታማነት ወደ 21 ኩንታል ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ሚኒስትሩ አብራርተዋል። በተጨማሪም በ 1 ነጥብ15 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ላይ የቡና ልማት ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን፣ ለዚህም ምርጥ የቡና ዘር አጠቃቀም፣ የተቀናጀ የአፈር ንጥረ-ነገር፣ የቡና ተክል ጥግግት፣ የገረዛና የጥላ ዛፍ አያያዝ፣ የተቀናጀ የተባይ መከላከል፣ የመስኖ፣ የማዳበሪያ እንዲሁም የተሻሻለ የምርት አሰባሰብና የዕድሳት ሥራዎችን ያካተቱ ዘጠኝ የትኩረት መስኮች ተለይተው ወደ ሥራ መግባታቸውን አመልክተዋል። ይህ አዲሱ የቡና ልማት ኢኒሼቲቭ አርሶ አደሮችን፣ የማህበራትንና የባለሙያዎችን ግንዛቤና አቅም ለማሳደግ ሰፊ የንቅናቄ ሥራዎችን እንደሚከናውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በቡና ወጪ ንግድ ከአፍሪካ ቀዳሚና ከዓለም 3ኛዋ ትልቅ ላኪ ሀገር በመሆን ያሳየችው እመርታ፣ የዘርፉን ታላቅ የምጣኔ-ሀብት አቅም በተጨባጭ የሚያሳይ ነው። ለዚህ ደግሞ ላለፉት ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ምህዳር በማስተካከል ረገድ የራሱን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ይታወቃል። በዚህም መርሃ-ግብሩ በተጀመረበት 2011 ዓ.ም 600 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የተተከለው የቡና ችግኝ በየዓመቱ እያደገ በመሔድ በ2017 ዓ.ም ላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሸፈን ተችሏል። ይሄ በመሆኑም የቡና ምርታማነት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል። በ2011 ዓ.ም. ግማሽ ሚሊዮን ቶን የነበረው ዓመታዊ የቡና ምርት 2017 ዓም ላይ ወደ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ምርት ማግኘት በመቻሉ ኢኮኖሚው ላይ ያለውን ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ማስቀጠል ችሏል። በመሆኑም፣ የተያዘውን የተቀናጀ የልማት ስትራቴጂ በተግባር በመተርጎም የቡናን ምርት በጥራትና በብዛት ማሳደግ፣ የሀገሪቱን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት ከመደገፍ ባለፈ የኢትዮጵያን ቡና የወደፊት ጉዞ እና ዓለም አቀፋዊ መሪነት እጅግ አስተማማኝ ያደርገዋል።
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዞ አንዱ መገለጫ -መሶብ
Aug 12, 2026 331
(በሙሴ መለሰ) የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች መመላለስ፣ የወረቀት ክምርና ረጅም ሰልፍ የኢትዮጵያውያን የቆየ የዕለት ተዕለት ፈተና ነበር። ይህንን የዜጎች እንግልት በዘላቂነት ለመቅረፍ እና አሰራርን ለማዘመን ታስቦ የተመሠረተው መሶብ የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል። የተቀናጀው የ"አዲስ መሶብ" ሱፐር አፕ (Super App) ዲጂታል መድረክ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ወደ ሙሉ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። የመሶብ ዋና ዓላማ ተበታትነው የነበሩ ልዩ ልዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ አጋዥነት በአንድ ጣሪያ ስር ማገናኘት ነው። ዜጎች ጊዜና ገንዘባቸውን ሳይባክኑ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ፣ የሰዎችን ቀጥተኛ ንክኪ በመቀነስ ሙስናና ብልሹ አሰራርን መዋጋት፣ እንዲሁም ግልጽነትን ማስፈን የተቋሙ መሠረታዊ ምሰሶዎች ናቸው። በረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ደግሞ እያንዳንዱ ዜጋ በብሔራዊ የፋይዳ (Fayda) መታወቂያው ብቻ በመጠቀም ሁሉንም የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ አካውንት እንዲያገኝ ማድረግ እና ሥርዓቱን ለአፍሪካ ሀገራት እንደ መሪ ተሞክሮ ማቅረብን ያለመ ነው። ይህ የዲጂታል መድረክ እና አጠቃላይ የቴክኖሎጂ ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሀገር በቀል እውቀት የበለጸገ ሲሆን፣ ጥቅም ላይ የዋሉት የሶፍትዌር ቴክኖሎጂዎች ለሁሉም ክፍት የሆነ (Open-source) መሆናቸው ተቋሙን ከከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ አድኖታል። በማዕከላቱ ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች ጥብቅ የሆነ የምልመላ ፈተና እና ልዩ ስልጠናዎችን አልፈው የሚገቡ በመሆናቸው የአገልግሎት ጥራቱ ከብልሹ አሰራር የፀዳ እንዲሆን አስችሏል። መጀመሪያ ላይ በ12 ተቋማትና በ41 አገልግሎቶች ብቻ የተጀመረው ይህ ዘመናዊ አሰራር፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እያሳየ ባለው ፈጣን እድገት በአሁኑ ወቅት የትስስር አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችሏል። አሁን ባለው ተጨባጭ ቁመና መሶብ 27 ዋና ዋና የመንግሥት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መስመር ማገናኘት የቻለ ሲሆን፣ እነዚህ ተቋማት በአንድ ላይ በመቀናጀት ከ288 በላይ የተለያዩ ዲጂታል አገልግሎቶችን በጥራትና በፍጥነት እያቀረቡ ይገኛሉ። ተገልጋዮች እንደ ፓስፖርት፣ ውክልና፣ የንግድ ፈቃድ እና የሰነዶች ማረጋገጫ ያሉ ወሳኝ ጉዳዮቻቸውን በአንድ ማዕከል ወይም በሞባይል መተግበሪያቸው ማከናወን ይችላሉ። ይህንን ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ100 በላይ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ማዕከላት የተቋቋሙ ሲሆን፣ እስካሁንም ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በማስተናገድ የአገልግሎት እርካታውን በፌዴራል ደረጃ ወደ ከ98 በመቶ በላይ ማድረስ ተችሏል። በቅርብ ቀናት ውስጥ የወጡ አዳዲስ ወቅታዊ መረጃዎች ደግሞ ተቋሙ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ እና ተለዋዋጭ እያደረገው መሆኑን ያሳያሉ። በቀን የሥራ ሰዓት መስተናገድ ለማይችሉ ሠራተኞችና ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ከተለመደው የሥራ ሰዓት ውጭ የምሽት አገልግሎት (Night Service) በይፋ ተጀምሯል። ከዚህ በተጨማሪ ወደ ማህበረሰቡ በቀጥታ በመሄድ አገልግሎት የሚሰጡት እና የራሳቸውን ኃይል በከፊል ከፀሐይ ብርሃን የሚያመነጩት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ አውቶቡሶች (Mobile Mesob Bus) በተለይ ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች የቤት ለቤት አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። የጤናው ዘርፍ አገልግሎቶችንም ለማካተት ከቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ጋር አዲስ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ ወደ ሀገር ለሚገቡ ባለሃብቶችና ዳያስፖራዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በቦሌ ዓለም አቀፍ አየውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ማዕከል እየተገነባ ይገኛል። በአዲስ አበባ ከተማም ከ480 በላይ የአገልግሎት መስኮቶች የሚኖሩት አንድ ግዙፍ ማዕከላዊ የኮምፕሌክስ ሕንፃ ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ ነው። “ዩኒፋይድ መሶብ” የተሰኘው የኦንላይን መድረክ ዜጎች በሞባይል ስልካቸው የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችል ሥርዓትም ተግባራዊ ሆኗል። በአሁኑ ወቅት መሶብ ከሀገር ውስጥ አልፎ ዓለም አቀፍ ትኩረትን እየሳበ ይገኛል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቤኒን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን ማዕከሉን በይፋ የጎበኙ ሲሆን፣ መሶብ ለአፍሪካ ሀገራት በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመንግሥት አገልግሎት ሥርዓት ለመገንባት እንደ ትልቅ የምርጥ ተሞክሮ ማሳያ እየተወሰደ ነው። በቀጣይም ከጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ጋር በዲጂታል አገልግሎት ዙሪያ የጋራ ትስስር በመፍጠር የአህጉር አቀፍ የዲጂታል ሥርዓት የመገንባት ስትራቴጂ ተነድፎ እየተሰራ ይገኛል። በአጠቃላይ መሶብ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን እና የሕዝብን እንግልት በመቀነስ ረገድ ውጤታማነቱን በተግባር ያረጋገጠ ስኬታማ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማሳያ ነው።
ወዳጅነት ፓርክ ፦ የመደመር እሴት ማሳያ
Aug 11, 2026 244
በሙሴ መለሰ በአዲስ አበባ መሐል የሚገኘው የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት ስምንት ዓመታት ከተገነቡት የመጀመሪያዎቹ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች አንዱ ነው። ይህ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውና 56 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ባለው የ“ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት” (Beautifying Sheger Project) ስር የተከናወነ ነው። ፕሮጀክቱ በሁለት ዋና ዋና ምዕራፎች ተከፍሎ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ሊጠናቀቅ ችሏል። ኢትዮጵያ የጀመረችው ይህ የከተማ ውበትና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ የውበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ሀብት ፈጣሪ መሆኑንም በተግባር ያረጋገጠ ህያው ማሳያ ነው። የወዳጅነት አደባባይ የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሂደት በ2011 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የቆሻሻ ማጠራቀሚያና ክፍት ቦታ የነበረውን ስፍራ ወደ ዘመናዊ አረንጓዴ ሥነ-ምህዳር ለመቀየር ያለመ ነበር። ግንባታው በ11 ወራት ብቻ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ በጳጉሜ 2012 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በቀድሞዋ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል። ይህ ክፍል 32 ሄክታር መሬት በማልማት፣ አሳ እና ዳክዬዎች የሚቀዝፉበት ሰው ሠራሽ ሐይቅ፣ ትልቅ አደባባይ (Square)፣ እና 1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻን መልሶ ማቋቋምን ያካተተ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ለምሽት መዝናኛ የሚሆን ማራኪ የፏፏቴ ላይ የብርሃን ትርኢት (Dancing Fountain)፣ ከ16 በላይ የውጪ ላይ ስብሰባ ማካሄጃ ቦታዎች (Event Venues)፣ የሰርግ አፀዶች፣ ካፌዎች፣ የፎቶ ስቱዲዮዎች እና ጠዋት ጠዋት የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ሩጫ ለማድረግ ምቹ የሆኑ የተከለሉ መንገዶችን ይዟል። ምዕራፍ አንድ ከተመረቀ በኋላ ወዲያውኑ የሁለተኛው ምዕራፍ (Friendship Park 2) የዲዛይንና የዝግጅት ሥራዎች ተጀምረዋል። በግንባታው ወቅት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም፣ ከሌላ ቦታ የተሰባሰቡ ከ4ሺህ በላይ አገር በቀል ትልልቅ ዛፎች (Indigenous trees) መጥተው በቦታው ላይ በተሳካ ሁኔታ እንዲተከሉ ተደርጓል። ግንባታው በጥቅምት 2015 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተመርቋል። 16 ሄክታር መሬት የሸፈነው ይህ ክፍል ከአብርሆት ቤተ-መጽሐፍት ፊት ለፊት የሚገኝ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ለሕፃናት፣ ለታዳጊዎችና ለቤተሰብ ስፖርታዊ መስተጋብር ተለይቶ የተገነባ ነው። በውስጡም እጅግ ዘመናዊና ሰፊ የሕፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን (Playgrounds)፣ ታዳጊዎች እየተጫወቱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን የሚለማመዱበትን የሳይንስ ማዕከል፣ ትንንሽ የእግር ኳስ (Mini-football) እና የቅርጫት ኳስ (Basketball) ሜዳዎችን፣ የሩጫ ትራኮችን፣ ለወጣቶች ንባብ የሚሆኑ ቦታዎችን (Reading nooks) እና ከጎኑ ያለውን የሳይንስ ሙዚየም ግንባታን ያካተተ ሰፊ ይዘት አለው። የወዳጅነት ፓርክ ከብሔራዊ ቤተመንግሥት እስከ መስቀል አደባባይባለው አካባቢ የሚዘልቅ ዘመናዊ የሕዝብ መገልገያና መዝናኛ ማዕከል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ ይህ ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ ማስገኘት ችሏል። ይህም የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ራሳቸውን ችለው ከፍተኛ ገቢ ማመንጨት ከመቻል ባለፈ፣ በቱሪዝም ዘርፉ፣ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዘንድ ለበርካታ ዜጎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሰፊ የሥራ ዕድል እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እየፈጠረ ይገኛል። ከዚህ ኢኮኖሚያዊ እሴቱ ባሻገር፣ ፕሮጀክቱ የከተማ ነዋሪዎችን ማኅበራዊ ትስስር በከፍተኛ ደረጃ ያጠናክራል፤ የዜጎችን የኑሮ ጥራት፣ የጤና ሁናቴ እና ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ (Life style) ከማሻሻል አንጻርም የመደመር እሴት በተግባር መሬት ማወረዱንና የዜጎችን አገራዊ የባለቤትነት ስሜት በጽኑ የሚያሳድግ ትልቅ ማሳያ ነው። ፓርኩ ለጤና፣ ለአካል ብቃት፣ ለመዝናኛና ለንባብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ወጣቶች ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን በስፖርት፣ በዕውቀት ቀሰማና በሌሎች በጎ ነገሮች ላይ እንዲያሳልፉ ምቹ ከባቢ ፈጥሯል። በተጨማሪም ቦታው ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎችና ጎብኝዎች በየቀኑ በስፋት የሚገናኙበት ማዕከል መሆን ችሏል። በስፍራው ከቤተሰቦችና ሕፃናት፣ ከስፖርት ቡድኖችና ከሠርግ ተካፋዮች ጀምሮ እስከ ዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎች በከፍተኛ ቁጥር ይገኙበታል። ይህም ለሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች (Content Creators) ምቹ ከባቢ በመፍጠር፣ የአዲስ አበባን ዘመናዊና ማራኪ ገጽታ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት እንዲያስተዋውቁና የከተማዋን በጎ ስም ለዓለም እንዲያደርሱ ትልቅ ዕድል ከፍቷል። ይህ ፓርክ አዲስ አበባን ለሌሎች የክልል ከተሞች በአረንጓዴ ልማት፣ በጽዳትና በዘመናዊ የሕዝብ መገልገያዎች በሞዴልነት የሚጠቀስ ሲሆን፣ የከተማዋን የዲፕሎማሲያዊ መዲናነት ገጽታ ይበልጥ በማደስ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች፣ ለዲፕሎማቶችና ለዓለም አቀፍ እንግዶች በጣም ሳቢና ተመራጭ መዳረሻ አድርጓታል። ፓርኩ በከተማዋ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ውስጥ እየተገነቡ ላሉ ተመሳሳይ የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ቀዳሚ ማሳያ ሲሆን፣ እነዚህ አዳዲስ ቦታዎች እሴት የሚፈጥሩ፣ ዕድሎችን የሚያመቻቹ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያንን ባለቤትነት የሚያረጋግጡ ማዕከላት መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ያረጋግጣል።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 11803
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 21602
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14629
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20381
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 104157
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79173
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57569
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55152
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 39510
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 39332
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 38810
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 37429
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 104157
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 79173
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57569
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 55152
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በምክክር እንጂ በመሳሪያ ድምጽ ሀገር አይገነባም
Aug 8, 2026 511
ኢትዮጵያ የዛሬ ማንነቷና ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እዚህ እንድትደርስ በርካታ ውጣውረዶችን አልፋለች። በቀደመ ታሪኳም ዜጎች በራሳቸው የውስጥ ጉዳይ መስማማት ባለመቻል እርስ በእርስ ካደረጓቸው ግጭቶች ባለፈ የውጭ ሃይሎችም የራሳቸውን አሉታዊ ጫና ሲፈጥሩ ቆይተዋል፤ አሁንም ይህንኑ ለማስቀጠል ተላላኪዎቻቸውን ለመጠቀም ሲሞክሩ ይታያል። በአንድ ሃገር ውስጥ የማያግባቡ ጉዳዮች በየትኛውም አጋጣሚና የታሪክ ምዕራፍ ሊያጋጥሙ ይችላሉ። እነዚህን ችግሮች በሃይል ለመፍታት የሚደረገው የመሳሪያ ትንቅንቅ ግን አክሳሪና ዘመን እያለፈበትም ነው። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ሰላማዊ የእድገት ጉዞ ለማወክ የህዝቦቿን አንድነት ለመበጥበጥ ከቅርብም ሆነ ከሩቅ የሚመጡ ጠላቶች ጠፍተው አያውቁም። በየዘመናቱ የተሻገርናቸው የታሪክ ስብራቶችን ፣ የመብት ጥያቄዎችንና ሌሎችንም መነሻ በማድረግ በውስጥ ባንዳዎች እና በውጭ ባዳዎች አማካኝነት የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ለመክተት፣ የብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚደረጉ ሴራዎች ዛሬም ላይ ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት ተሰሚነትና ተጽዕኖ የሚያሳምማቸው ለዜጎቿን እኩል ተጠቃሚነትና ብልጽግና መረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚያስጨንቃቸው እነዚህ ሃይሎች በመብት ፣ በነጻነት፣ በዴሞክራሲ፣ በማንነትና በሌሎችም የሃሰት ትርክቶች መነሻነት በሩቅ ቢያቅታቸው በቅርብ የውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን እያደራጁ በጀት መድበው የጦር መሳሪያ አቅርበው ሀገር የማፍረስ ሙከራቸውን አላቋረጡም። በመደመር እሳቤ ሁሉንም በአንድ ላይ በማቀራረብና የጋራ ትርክቶችን በመገንባት ከልዩነት ይልቅ የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ዘላቂ ልማቷን መፃኢ ብሩህ ተስፋዋን ለማለምለም በሁሉም ዘርፍ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ተሳትፎ እየሰራች መሆኗም ምቾት ነስቷቸዋል። በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሔደ ያለውና ወርቃማው እድል ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ፣ የሚያስችሉ ወሳኝ ምዕራፎች ላይ ደርሷል ። በዚህ የምክክር ሒደት በሀገሪቱ የትኛውም ጥግ ያለ ዜጋ እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የተወከሉበት ፣ የብሔር፣ የፖለቲካ አመለካከትና የሃይማኖት ልዩነት የማያደናቅፉት ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እየተካሔደ ይገኛል። ጥያቄያችንን በጠብመንጃ አፈሙዝ እንፈታለን ያሉ ታጣቂዎችም ብረት በማስቀመጥ አጀንዳዎቻቸውን ይዘው ወደ ጠረጴዛው ቀርበዋል። ልክ ናቸው ሀገር ከሁሉም ነገር ትበልጣለችና ይሄንን ወርቃማ እድል ለመጠቀም ማሰብ ትክክለኛው ውሳኔ ነው። በትጥቅ ትግል ጥያቄያችንን እንመልሳለን በሚል ሽፋን የሌሎችን አጀንዳ ለማሳካት የሚደረግ ጥረት የሃገርና የትውልድ ጠባሳ ከማስቀመጥና የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው መገንዘብ ብልህነት ነው። የዚህ ምክክር ተሳታፊ/ተመካካሪ ከሆኑት የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) አመራር ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በዚህ ይስማማሉ ። ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ተስፋ የጣልንበት፣ በንግግር፣ በምክክር ሀገራችንን የምናስቀጥልበት፣ ሁሉም ተነጋግሮ ተመካክሮ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ከችግሮች ነፃ የሚያደርግበት ነው ይላሉ። ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚነጋገርበት፣ የሚመካከርበት እና በሃሳብ የበላይነት ጠንካራ ሃገር የሚፈጠርበት መልካም የታሪክ አጋጣሚ መሆኑንም ይናገራሉ። በምክክር፣ በድርድር የሕዝብን ጥያቄ በመመለስ ሀገርን የምናስቀጥልበትና የውጭ ኃይሎችን ጣልቃ ገብነት የምናስወግድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ነው ብለዋል። የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራር የቀድሞ ታጣቂ ጃል ሰኚም ይሄንኑ ሃሳብ ይጋራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ለዓመታት የቆዩ ልዩነቶችን ለመፍታት ሀገራዊ ምክክር መዘጋጀቱ ትልቅ እርምጃ እንደመሆኑ እሳቸውም ያላቸውን ሀሳብ በማንጸባረቅ እየመከሩ ይገኛሉ። እርሳቸውና ቡድናቸው ከዚህ ቀደም የትጥቅ ትግልን በመምረጥ ጫካ ገብተው እንደነበር አስታውሰው፤ ችግሮችን በመሳሪያ ከመፍታት ይልቅ በሰላማዊ የምክክር መድረክ መፍታት ጥሩ አማራጭ መሆኑን አምነው ወደ ሰላም መንገድ መምጣታቸውንም ተናግረዋል። ችግሮቻቸውን በምክክር የፈቱ ሀገራት በሁሉም ዘርፍ ዕድገታቸውን የሚያስቀጥሉ ሲሆኑ ወደ ትጥቅ ትግል ያመሩና ግጭት ውስጥ የገቡት ደግሞ በፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውድቀት ለከፋ ድህነት መዳረጋቸውን ጠቅሰዋል። የጦር መሣሪያ በመነቅነቅና ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ በመግባት የሚፈታ ችግር እንደሌለ የሚናገሩት ደግሞ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ(አብን) አመራሩ ተመካካሪ ጣሒር መሀመድ ናቸው። ጫካ ባለውና እዚህ ባለው ሰው መካከል ምንም ዐይነት የዜግነት ልዩነት እንደሌለ ገልጸው ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሃሳብ ለመታገል ልዩነቱን ለማቅረብ የፈለገ ሁሉም ዜጋ በምክክሩ የመሳተፍ ነጻነት እንዳለው ገልጸዋል። በሃገራዊ ምክክሩ ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሰላማዊ መድረክ መወያየት የተመረጠበት ዋና ምክንያት ዘላቂ ሰላም፣ አገራዊ መግባባት እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ ለማምጣት ነው:: የትጥቅ ትግል የዜጎችን ህይወት ያጠፋል፣ መሰረተ ልማቶችን ያወድማል፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድቀትንም ያመጣል: ፤ ሰላማዊ መድረክ ግን ያለምንም ደም መፋሰስ ሃሳብን በሃሳብ ለመሞገት እድል ይሰጣል:: በኃይል የሚመጣ ለውጥ ብዙውን ጊዜ አሸናፊና ተሸናፊን ስለሚፈጥር የቁስል እና የቂም ዑደትን ያስቀጥላል:: በሰላማዊ ውይይት የሚገኝ መፍትሄ ግን የሁሉንም ወገን ስጋት እና ፍላጎት ያገናዘበ በመሆኑ ዘላቂነት ይኖረዋል:: ሃገራዊ ምክክሩ የታጠቁ አካላትም ጭምር መሳሪያቸውን አስቀምጠው በሃሳብ እንዲፎካከሩ መንገድ ከፍቷል። ይህ ታሪካዊና ወርቃማ እድል ኢትዮጵያዊንን አግባብቶ ወደተረጋጋችና የበለጸገች ሃገር የሚመራ በመሆኑ ስኬታማነቱ አያጠራጥርም። ለእድለኛው ትውልድ ያጋጠመው ወርቃማው ስጦታ ሃገራዊ ምክክር የተቋቋመለትን ዓላማ ያሳካል።
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 1375
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም