መነሻ - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ከህብረተሰቡ ለሚነሱ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች በፍትሃዊነት አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው-የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ
Mar 27, 2023 46
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ) ከህብረተሰቡ ለሚነሱ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች በፍትሃዊነት አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኣባላት ከመራጭ ኅብረተሰብ የተነሱ ጥያቄዎችን በሚመለከት ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን፤ የመንገድ፣ የውሃና የመብራት ተደራሽነት ጥያቄዎች ከኀብረተሰቡ መነሳታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይም ከመብራት እና ከቴሌኮም አገልግሎት መቆራረጥ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ ምላሽ እንደሚሻም ተመላክቷል። የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ አለመጠናቀቅ ህብረተሰቡን አሁንም ለቅሬታ የዳረጉ ጉዳዮች መሆናቸው ተነስቷል። የፕላን እና ልማት ሚንስትሯ ዶክተር ፍጹም አሰፋ በዚሁ ወቅት መሰረተ ልማትን በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረው ጦርነት በመሰረተ ልማት አውታሮች ላይ ጉዳት ማድረሱንና ፕሮጀክቶች እንዲጓተቱ ማድረጉንም ጠቁመዋል፡፡ በቀጣይ መንግስት ይህን ለማስተካከል በትኩረት እየሰራ መሆኑን በማንሳት፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በበኩላቸው በመብራት መሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች አሁንም ለአገልግሎቱ መቆራረጥ ምክንያት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን የማዘመና የተባላሹ መስመሮች በመጠገን ተደራሽ እንዲሆን እየሰራ ነው ብለዋል። በቀጣይም ከህብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩም በአገር አቀፍ ደረጃ የቴሌኮም ኔትወርክ አቅምን የማሳደግ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። ኩባንያው የቴሌኮም ተደራሽነትን ለማስፋትና የአገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ የመሰረተ ልማት ማስፋፋትን ጨምሮ የጥገና ስራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ አብራርተውል፡፡ በበጀት ዓመቱ በአገር አቀፍ ደረጃ 320 የመንገድ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን ናቸው። ለግንባታ የሚሆኑ ጥሬ እቃዎች ዋጋ መናር አሁንም ዘርፉን እየፈተነው መሆኑን ጠቅሰው፤ ችግሩን በመቋቋም የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በጋምቤላ ክልል የውሃና የመሬት ሀብትን ለልማት በማዋል የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥ እየተሰራ ነው--የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ
Mar 27, 2023 64
ጋምቤላ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰፊ የውሃና የመሬት ሀብት ለልማት በማዋል የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ አስታወቀ። በአርብቶ አደር ፖሊሲና የማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ላይ የክልሉ አመራሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተወያይተዋል። የቢሮው ኃላፊ አቶ ኮንግ ጆክ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት መንግስት በአርብቶ አደር አካባቢዎች ያለውን የተፈጥሮ ሀብት ግምት ውስጥ ያስገባ ፖሊሲና ስትራቴጂ በመቅርጽ ወደ ሥራ መግባቱን ገልጸዋል። የተቀረጸው ፖሊሲ የክልሉን አርሶና አርብቶ አደሮች ኑሮ የሚለውጥና የሚያሻሽል በመሆኑ ለአመራሩ በቂ ግንዛቤ በማስያዝ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ ፒን ኡጁሉ በበኩላቸው፣ በክልሉ ያለውን ሰፊ የመሬትና የውሃ ሀብት በማልማት የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ በግንባታ ሂደትና ተገንብተው መጠነኛ ችግር ያለበችውን ስምንት የመስኖ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ በማስገባት ተጠቀሚ ለማድርግ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህም በተጨማሪ በክልሉ ከ30ሺህ ሄከታር በላይ መሬት ማልማት የሚያስችሉ 12 ከፍተኛና መካከለኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ጥናት እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል። ጥናቱ እየተካሄደ ያለው በክልሉ ቢሮ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስቴር ትብብር መሆኑን ገልጸዋል። የመስኖ ግብርና ልማቱ በቴክኖሎጂ እንዲደገፍ ሚኒስቴሩ 36 የእርሻ ትራክተሮችን ድጋፍ ማድረጉን ምክትል ቢሮ ኃላፊው አስታውቀዋል። በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስቴር የቆላማ አካባቢ ምርምር ዴስክ ኃላፊ አቶ አሸብር ደምለው በበኩላቸው መስሪያ ቤቱ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የአርብቶ አደሩንና ቆላማ አካባቢዎችን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተከናወኑት ሥራዎች በቂ ናቸው ባይባልም አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቁመው በቀጣይም ሚኒስቴሩ የጀመረውን ድጋፍ የማስተባበር ሥራ አጠናከሮ ይቀጥላል ብለዋል። በቢሮውና በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ትብብር በተዘጋጀው የአርብቶ አደር ፖሊሲና የማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ውይይት ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳተፈዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለሕዝብ ጥያቄ መፍትሔን የሚያመነጭ አመራርን መፍጠር ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል - የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
Mar 27, 2023 52
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ) የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ በመረዳት ለህዝብ ጥያቄ መፍትሔን የሚያመነጭ አመራርን መፍጠር ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ሲል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳሰበ። በምክር ቤቱ የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአካዳሚውን የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ገምግሟል። በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የእቅድ፣ በጀትና ሪፎርም ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ጫኔ የተቋሙን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። በዚህም በግማሽ ዓመቱ ማዕከሉ በአዲስ መልክ መቋቋሙን ተከትሎ ተልዕኮውን በማሳካት ረገድ በርካታ ሥራዎችን አከናውኗል። በተለይም አጫጭር ሥልጠናዎችን መስጠት፣ የውጪ የትምህርት እድሎችን ማመቻቸት፣ የፖሊሲ ምርምሮችን ማካሄድና ተተኪ አመራሮችን ማብቃት ተጠቃሽ ናቸው። የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንን ጨምሮ ሥልጠናዎችን በበይነ-መረብ ለማካሄድ የሚያስችል ፕሮጀክት ተግባራዊ ማድረጉም እንዲሁ። ይሁን አንጂ ተቋሙ ከሚጠበቅበት ውጤት አኳያ በቂ ሥራዎች ተሰርተዋል ተብሎ እንደማይታመን አቶ ምትኩ አብራርተዋል። የቋሚ ኮሚቴው አባላት በበኩላቸው ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ ጥያቄና አስተያየት ሰንዝረዋል። በተለይም ከተቋሙ ስያሜ አኳያ ፓናፍሪካኒዝምን አጉልቶ በማሳየትና ተደራሽነቱን በማስፋት ረገድ ውስንነቶች እንዳሉ አንስተዋል። በፌዴራል፣ በክልልና የከተማ አስተዳደር አመራሮችን አቅም ከማሳደግ አኳያ ጎልተው የሚታዩ ሥራዎች አለመከናወናቸውንም የቋሚ ኮሚቴው አባላት ገልጸዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ በበኩላቸው ማዕከሉ በይፋ ሥራውን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ በርካታ ሥራዎችን ማከናወኑ አይዘነጋም። በተለይም ደግሞ የተቋሙን አሰራር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ያደረገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የእቅድ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ መሆኑ ደግሞ በትኩረት ሊታይና ሊፈተሽ እንደሚገባ ሰብሳቢው አንስተዋል። የሰው ሃይል አቅሙን ማደራጀት፣ የሥልጠና ብቃት ማረጋገጫ ተግባር ላይ መዋሉን ክትትል ማድረግና ወቅታዊና አስቸኳይ የሥልጠና ማንዋሎችን ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ ሌላኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን አብራርተዋል። በዋናነት የአገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገነዘብና ለሕዝብ ጥያቄ መፍትሄን የሚያመነጭ አመራርን መፍጠር ላይ አጽንዖት መሰጠት ያስፈልጋል ብለዋል። የአካዳሚው ፕሬዝዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ አካዳሚውን በአዲስ መልክ የማደራጀት ሥራው ጊዜ የወሰደ በመሆኑ በሚፈለገው ልክ እቅዱን ማሳካት አልተቻለም ብለዋል። ተደራሽነትን በማስፋት ረገድ በቂ ሥራዎች አለመሰራታቸውን ገልጸው በግማሽ ዓመቱ በሦስት የአፍሪካ አገራት ለሚገኙ የውጭ አገራት ሙያተኞች ሥልጠና ተሰጥቷል ነው ያሉት። የተልዕኮ መመሳሰል ካለባቸው ተቋማት ጋር በምን መልኩ መሥራት እንደሚያስፈልግ የሚደነግግ የሕግ ማዕቀፍ አለመኖሩም አካዳሚው ተልዕኮውን በአግባቡ እንዳይወጣ እንቅፋት ሆኖበታል ብለዋል። ያም ሆኖ አሁንም ቋሚ ኮሚቴው የሰጠውን አስተያየት መነሻ በማድረግ አካዳሚው የማስተካከያ ሥራዎችን በመሥራት ለላቀ ውጤት እንደሚተጋ ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
አስፈጻሚ አካላት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ የኅብረተሰብ ጥያቄዎች ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Mar 27, 2023 57
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ አስፈጻሚ አካላት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ የኅብረተሰብ ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አሳሰቡ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመራጭ ኅብረተሰብ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል። ምክር ቤቱ በዓመት ሁለት ጊዜ ከመረጠው ሕዝብ ጋር ውይይት የሚያደርግ መሆኑ በውይይቱ ተገልጿል። ተመራጮቹ በቅርቡ ከመራጩ ሕዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት የልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሠላምና ደኅንነት እንዲሁም የኑሮ ውድነትን የተመለከቱ ጥያቄዎች ተነስተዋል፤ እነዚህም ጥያቄዎች ለሚመለከተው አስፈፃሚ አካላት ቀርበዋል። የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ መሠረት ኃይሌ በየምርጫ ክልሉ በነበረው ውይይት የተነሱ ጉዳዮችን በተመለከተ ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጓል። በዋናነት በውይይቶቹ የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ቀዳሚ ሲሆን ሌላኛው ከኑሮ ውድነት ጋር የተነሱ ጥያቄዎች አብዛኛውን ድርሻ መያዛቸውን ተናግረዋል። የኑሮ ውድነትና ሰው ሰራሽ የምርት እጥረት ኅብረተሰቡን እየፈተነ እንደሚገኝም ተመላክቷል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚንስትሩ ገብረመስቀል ጫላ የምርት እንቅስቃሴ ላይ ሲስተዋል የነበረው መስተጓጎል አሁን ላይ በተወሰዱ እርምጃዎች ምርቶች በሚፈለገው መጠን መንቀሳቀስ መጀመራቸውን ተናግረዋል። እንዲሁም በመላው አገሪቱ ባሉ የእሁድ ገበያዎች ሰፋ ያሉ የግብርና ምርቶች ቀርበው ለኅብረተሰቡ ተደራሽ መሆናቸውን ገልጸዋል። በሰው ሰራሽ የዋጋ ንረትና ሕገ-ወጥ ንግድ ላይ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ስለመሆኑ ተናግረዋል። ይህንን የኑሮ ውድነት ችግር መቅረፍ በአንድ ተቋም ብቻ የሚፈታ አለመሆኑን የገለጹት ሚንስትሩ ከተለያየ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሚተገበር የጋራ እቅድ ተዘጋጅቷል ብለዋል። ከኢኮኖሚ አሻጥሮች ጋር በተየያዘ ችግሮቹ እየተገመገሙ እርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁመዋል። በቀጣይ መንግሥት ቁጥጥር የሚያደርግባቸው ምርቶች የመለየት ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አመላክተዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አስፈጻሚ አካላት በአጭር ጊዜ መፈታት ያለባቸውን ችግሮች በቅድሚያ መፍታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። እንዲሁም ጊዜ የሚወስዱ ሥራዎች በአግባቡ ለኅብረተሰቡ ማስገንዘብ እንደሚገባ ተናግረዋል። አስፈጻሚዎች በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ የኅብረተረሰብ ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። እንዲሁም የፌደራልና የክልል አመራሮች እነዚህን ችግሮች ለመፍታት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
መንግስት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል-ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ
Mar 27, 2023 71
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ መንግስት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ገለጹ። የፍትሕ ስርዓቱን ብልሽቶች ማስተካከል አላማ ያደረገ የሶስት ዓመት የማሻሻያ ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በየካቲት ወር 2015 በምርጫ ክልላቸው በመገኘት ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። የምክር ቤቱ አባላት በውይይቶቹ ከሕብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን የያዘ ሪፖርት ዛሬ ለአስፈጻሚ አካላት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም በሁሉም አካባቢዎች በተደረጉ ውይይቶች የሰላም እና ጸጥታ ችግርን ሕብረተሰቡ ማንሳቱን ገልጸዋል። የዜጎች ተዘዋውሮ የመስራት መብት አለመከበር ጉዳይ መፍትሔ እንዲሰጠው እና የሕግ አስፈጻሚው አካል ሰላምን በሚያደፈርሱ አካላት ላይ እርምጃ በመውሰድ አስተማማኝ ሰላምን እንዲያሰፍንም አሳስበዋል። በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ከአገልግሎት አሰጣጥ አንጻር ያሉ ብልሹ አሰራሮች እንዲቀረፉ የምክር ቤት አባላቱ የሕዝብን ጥያቄ ዋቢ አድርገው አቅርበዋል። የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በተለያዩ አካባቢዎች ግጭት በመቀስቀስ፣ በመሳተፍና በማስተባበር የተጠረጠሩ በርካታ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በሕግ እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት በሃይማኖትና በብሔር ሽፋን ግጭት ለመቀስቀስ የሚሞክሩና የአገርን ሰላም የሚያውኩ አካላት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥና በሁሉም አካባቢዎች " ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን በትኩረት እየሰራ ነው" ብለዋል። ዶክተር ጌዲዮን አክለውም የፍርድ ቤት ጉዳዮችን ጨምሮ በፍትሕ ተቋማት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የፍትሕ ስርዓቱ ላይ ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተለይም አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሙስና ተግባር የሚፈጽሙ አካላት ላይ ቀጣይነት ያለው እርምጃ የመውሰድና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት። በሌላ በኩል የፍትህ ስርዓቱን ለማዘመን በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት የሚተገበር የማሻሻያ ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። ፍኖተ ካርታውን ወደስራ ለማስገባት እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ገልጸው የፍትሕ ስርዓቱ የሰው ኃይል ብቃት ላይም ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጄነራል ዘላለም መንግስቴ ባለፉት ስድስት ወራት ጠንካራ የሕግ ማስከበር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በዚህም በተለያዩ አካባቢዎች ግጭት በመቀስቀስ የሰላምና ፀጥታ ችግር የፈጠሩ ግለሰቦች ላይ እርምጃ መወሰዱን ጠቅሰዋል። የጸጥታ ስጋቶችን በአግባቡ የመምራት አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ መምጣቱን ገልጸው፤ የዜጎችን ሰላምና የሀገርን ልማት የሚያስተጓጉሉ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ላይ ጠንካራ እርምጃ ይወሰዳል ነው ያሉት ኮሚሽነር ጄነራሉ።
ፖለቲካ
አስፈጻሚ አካላት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ የኅብረተሰብ ጥያቄዎች ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Mar 27, 2023 57
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ አስፈጻሚ አካላት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ የኅብረተሰብ ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አሳሰቡ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመራጭ ኅብረተሰብ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል። ምክር ቤቱ በዓመት ሁለት ጊዜ ከመረጠው ሕዝብ ጋር ውይይት የሚያደርግ መሆኑ በውይይቱ ተገልጿል። ተመራጮቹ በቅርቡ ከመራጩ ሕዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት የልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሠላምና ደኅንነት እንዲሁም የኑሮ ውድነትን የተመለከቱ ጥያቄዎች ተነስተዋል፤ እነዚህም ጥያቄዎች ለሚመለከተው አስፈፃሚ አካላት ቀርበዋል። የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ መሠረት ኃይሌ በየምርጫ ክልሉ በነበረው ውይይት የተነሱ ጉዳዮችን በተመለከተ ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጓል። በዋናነት በውይይቶቹ የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ቀዳሚ ሲሆን ሌላኛው ከኑሮ ውድነት ጋር የተነሱ ጥያቄዎች አብዛኛውን ድርሻ መያዛቸውን ተናግረዋል። የኑሮ ውድነትና ሰው ሰራሽ የምርት እጥረት ኅብረተሰቡን እየፈተነ እንደሚገኝም ተመላክቷል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚንስትሩ ገብረመስቀል ጫላ የምርት እንቅስቃሴ ላይ ሲስተዋል የነበረው መስተጓጎል አሁን ላይ በተወሰዱ እርምጃዎች ምርቶች በሚፈለገው መጠን መንቀሳቀስ መጀመራቸውን ተናግረዋል። እንዲሁም በመላው አገሪቱ ባሉ የእሁድ ገበያዎች ሰፋ ያሉ የግብርና ምርቶች ቀርበው ለኅብረተሰቡ ተደራሽ መሆናቸውን ገልጸዋል። በሰው ሰራሽ የዋጋ ንረትና ሕገ-ወጥ ንግድ ላይ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ስለመሆኑ ተናግረዋል። ይህንን የኑሮ ውድነት ችግር መቅረፍ በአንድ ተቋም ብቻ የሚፈታ አለመሆኑን የገለጹት ሚንስትሩ ከተለያየ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሚተገበር የጋራ እቅድ ተዘጋጅቷል ብለዋል። ከኢኮኖሚ አሻጥሮች ጋር በተየያዘ ችግሮቹ እየተገመገሙ እርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁመዋል። በቀጣይ መንግሥት ቁጥጥር የሚያደርግባቸው ምርቶች የመለየት ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አመላክተዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አስፈጻሚ አካላት በአጭር ጊዜ መፈታት ያለባቸውን ችግሮች በቅድሚያ መፍታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። እንዲሁም ጊዜ የሚወስዱ ሥራዎች በአግባቡ ለኅብረተሰቡ ማስገንዘብ እንደሚገባ ተናግረዋል። አስፈጻሚዎች በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ የኅብረተረሰብ ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። እንዲሁም የፌደራልና የክልል አመራሮች እነዚህን ችግሮች ለመፍታት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
መንግስት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል-ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ
Mar 27, 2023 71
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ መንግስት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ገለጹ። የፍትሕ ስርዓቱን ብልሽቶች ማስተካከል አላማ ያደረገ የሶስት ዓመት የማሻሻያ ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በየካቲት ወር 2015 በምርጫ ክልላቸው በመገኘት ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። የምክር ቤቱ አባላት በውይይቶቹ ከሕብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን የያዘ ሪፖርት ዛሬ ለአስፈጻሚ አካላት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም በሁሉም አካባቢዎች በተደረጉ ውይይቶች የሰላም እና ጸጥታ ችግርን ሕብረተሰቡ ማንሳቱን ገልጸዋል። የዜጎች ተዘዋውሮ የመስራት መብት አለመከበር ጉዳይ መፍትሔ እንዲሰጠው እና የሕግ አስፈጻሚው አካል ሰላምን በሚያደፈርሱ አካላት ላይ እርምጃ በመውሰድ አስተማማኝ ሰላምን እንዲያሰፍንም አሳስበዋል። በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ከአገልግሎት አሰጣጥ አንጻር ያሉ ብልሹ አሰራሮች እንዲቀረፉ የምክር ቤት አባላቱ የሕዝብን ጥያቄ ዋቢ አድርገው አቅርበዋል። የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በተለያዩ አካባቢዎች ግጭት በመቀስቀስ፣ በመሳተፍና በማስተባበር የተጠረጠሩ በርካታ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በሕግ እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት በሃይማኖትና በብሔር ሽፋን ግጭት ለመቀስቀስ የሚሞክሩና የአገርን ሰላም የሚያውኩ አካላት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥና በሁሉም አካባቢዎች " ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን በትኩረት እየሰራ ነው" ብለዋል። ዶክተር ጌዲዮን አክለውም የፍርድ ቤት ጉዳዮችን ጨምሮ በፍትሕ ተቋማት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የፍትሕ ስርዓቱ ላይ ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተለይም አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሙስና ተግባር የሚፈጽሙ አካላት ላይ ቀጣይነት ያለው እርምጃ የመውሰድና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት። በሌላ በኩል የፍትህ ስርዓቱን ለማዘመን በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት የሚተገበር የማሻሻያ ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። ፍኖተ ካርታውን ወደስራ ለማስገባት እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ገልጸው የፍትሕ ስርዓቱ የሰው ኃይል ብቃት ላይም ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጄነራል ዘላለም መንግስቴ ባለፉት ስድስት ወራት ጠንካራ የሕግ ማስከበር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በዚህም በተለያዩ አካባቢዎች ግጭት በመቀስቀስ የሰላምና ፀጥታ ችግር የፈጠሩ ግለሰቦች ላይ እርምጃ መወሰዱን ጠቅሰዋል። የጸጥታ ስጋቶችን በአግባቡ የመምራት አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ መምጣቱን ገልጸው፤ የዜጎችን ሰላምና የሀገርን ልማት የሚያስተጓጉሉ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ላይ ጠንካራ እርምጃ ይወሰዳል ነው ያሉት ኮሚሽነር ጄነራሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት የመንግስትን የስድስት ወር ሪፖርት ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ
Mar 27, 2023 129
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት የመንግስትን የስድስት ወር አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ፡፡ ምክር ቤቱ ነገ በሚያካሂደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሚቀርበውን ሪፖርት ያዳምጣል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ የተለያዩ ወቅታዊና ሀገራዊ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡
ከመራጩ ህብረተሰብ በተነሱ ጉዳዩች ላይ ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው
Mar 27, 2023 98
አዲስ አበባ መጋቢት 18/ 2015 (ኢዜአ) በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመራጩ ህብረተሰብ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። ምክር ቤቱ በዓመት ሁለት ጊዜ ከመረጠው ሕዝብ ጋር ውይይት የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም በየካቲት ወር ባደረገው የሕዝብ ውክልና ስራ ከመራጩ ሕዝብ ጋር በተደረገ ውይይት የልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሠላም እና የኑሮ ውድነትን በተመለከተ ከመራጩ ሕዝብ የተነሱ ጥያቄዎችን ለሚመለከተው አስፈፃሚ አካላት መቅረቡ ተገልጿል። ይህንኑ በተመለከተ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ መሠረት ኃይሌ በየምርጫ ክልሉ የነበረው የውይይት ሂደት በተመለከተ ሪፖርት አቅርበው ውይይት እየተደረገ መሆኑን ከምክርቤቱ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
"በቀጣይ የብልጽግና ፓርቲ ዋናው የቤት ሥራ ነፃነትን በአግባቡ መጠቀም እና ማስተዳደር ላይ መሥራት ነው"-የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ
Mar 27, 2023 102
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ)፦ "በቀጣይ የብልጽግና ፓርቲ ዋናው የቤት ሥራ ነፃነትን በአግባቡ መጠቀም እና ማስተዳደር ላይ መሥራት ነው" ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ተናገሩ፡፡ "ድሎችን ማፅናት እና ፈተናዎችን መሻገር" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ወቅታዊ እና ታሪካዊ የአመራር ተልእኮ መድረክ በሀገራዊ የሰላም፣ የፀጥታ እና የልማት ጉዳዮች ላይ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው ውይይት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋናው ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ከተሳታፊ አመራሮች ለተነሡ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የኑሮ ውድነትን፣ የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ መንግሥታዊ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮችን በሚመለከት ብልጽግና ፓርቲ በትኩረት እንደሚሠራ አበክረው ገልጸዋል። ብልጽግና ፓርቲ አስቀድሞ የጀመራቸውን መርህን መሠረት ያደረጉ ተቋማዊ አሠራሮችን አጠናክሮ በማስቀጠል የፓርቲውን ሕዝባዊ ቅቡልነት ማሳደግ እና ጠንካራ መንግሥታዊ አቅም መፍጠር እንደሚገባም ጠቅሰዋል። ይህንንም ለማጠናከር አመራሩ የአመለካከት እና የተግባር አንድነቱን በማጠናከር በኅብረ ብሔራዊ አንድነት በተሰናሰለ ወጥ ሀገራዊ እሳቤ አቅም መሆን እንደሚገባው አንሥተዋል። የብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካዊ እሳቤዎች ኢትዮጵያዊ መሠረት ያላቸው እና የሀገራችንን እና የሕዝባችንን ችግር ፈቺዎች እንዲሆኑ ማድረግ፣ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ማሳደግ እና የሕዝቡን ፖለቲካዊ ሞጋችነት እና የልማት ተሳትፎ እንዲሁም ተጠቃሚነት በማሳደግ ቅቡልነትን ማሳገድ እንደሚገባም ማብራሪያ ሰጥተዋል። በአጠቃላይ ብልጽግና ፓርቲ መላ መዋቅራዊ አቅሙን ፈትሾ የሚታዩ የአመራር የአቅም ጉድለቶችን አርሞ፣ ውስጣዊ ብልሽቶችን አክሞ እና መርሕን መሠረት ባደረገ አግባብ ተግባራት በማሳለጥ የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ እና ዕድገት በማስቀጠል ሕዝባዊ ቅቡልነትን ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ እንደ ሀገር የመጣውን ነፃነት ከመጠቀም ጋር ሰፊ ክፍተት እንዳለ እና ነፃነትን ማክበር እና ማስከበር በሚመለከት ብልጽግና ፓርቲ የሚደራደርበት ጉዳይ እንዳልሆነ አሳስበዋል። እንደመሪ ፓርቲ ነፃነትን በአግባቡ መጠቀምና ማስተዳደር ላይ መሥራት እንደሚገባም አክለው ገልጸዋል። በተመሳሳይ ነፃነትን በፓርቲው ውስጥ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ እና የፓርቲው አመራር እና አባል ተገቢ ነፃነት ተጎናፅፎ ሐሳቡን ያለተፅዕኖ እያራመደ መቀጠል እንዳለበት በአፅንኦት አስቀምጠዋል። እንደ ሀገር የዴሞክራሲ፣ የፍትሕ እና የዳኝነት ተቋማት በነፃነት እና በገለልተኝነት ሥራቸውን አጠናክረው መሥራት እንደሚገባቸውም ለተሳታፊ አመራሮች ማንሣታቸውን ከፓርቲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የመደመር እሳቤ ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለምን መጻዒ ዘመን የተሻለ ለማድረግ ሁሉም ሊተገብረው የሚገባ መርህ ነው...የህንድ ባለሃብቶች
Mar 25, 2023 157
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2015 (ኢዜአ) የመደመር እሳቤ ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለምን መጻዒ ዘመን የተሻለ ለማድረግ ሁሉም ሊተገብረው የሚገባ መርህ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የሕንድ ባለሃብቶች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ የአስደናቂ ታሪክ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያ በመምራት ሂደት በተለይ የትውልድ ቀረጻ ላይ ማተኮራቸውን አድንቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን እና የትውልዱን መጻዒ ብሩህ ተስፋ የሚተልሙ መደመር፣ የመደመር መንገድ እና የመደመር ትውልድ የተሰኙ ሦስት መጻሕፍትን አበርክተዋል። ሦስቱም መጻሕፍት ማጠንጠኛ 'መደመር' ቢሆንም የመደመር እሳቤው ምንነት፣ ስለትግበራ መንገዱ እና ስለትውልዱ ትግበራ ወሰን በተለያዬ ዐውድ የሚያትቱ ናቸው። በቅርቡ የተመረቀው 'የመደመር ትውልድ' የተሰኘው ሶስተኛ መፅሓፋቸው የእንግሊዝኛ ቅጂ ለዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እና ለውጭ ባለሃብቶች በታደሙበት የማስተዋወቅ መድረክ ተካሂዷል። በኢትዮጵያ የሕንድ ባለሃብቶች ፎረም ምክትል ሰብሳቢ ራጂቭ ሻርማ እንዳሉት፤ መፅሐፉ የመደመር ትውልድ ከትናንት እንዲማርና የራሱን አቅሙን አሰባስቦ የተሻለች ሀገር እንዲገነባ መንገድ ያሳያል። የመደመር እሳቤ ዓለም አቀፋዊ መርሆን የሚያስተጋባ በመሆኑ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለተቀረው ዓለም የሚበጅ መሆኑንም እንዲሁ። አፍሪካውያን ከቀደመ ታሪካቸው እንዲማሩ፣ እርስ በርስ እንዲተዋወቁ ብሎም ወደ ፊት ጠንካራ አህጉር መገንባት የሚያስችል አቅማቸውን ወደ ተግባር እንዲለውጡ መንገድ የሚጠቁም መሆኑንም ተናግረዋል። የህንድ የቢዝነስ ፎረም አባል ካውሸል ሼድ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ጥንታዊትና አኩሪ ታሪክ ያላት እና መልከ ብዙ ውጣ ውረዶችን ያሳለፈች ሀገር መሆኗን አውስተዋል። የዘመኑ ትውልድም ከትናንት ታሪክ ቁም ነገሮችን ቀስሞ፤ በመደመር እሳቤ የተሻለ ነገን መገንባት እንደሚችል መመላከቱን ጠቁመዋል። ከቅደመ አያቶቻቸው ጀምሮ ቤተሰቦቻቸው ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ መኖራቸውን የሚናገሩት ሕንዳዊ ባለሀብት ሀርሺ ኮታሪ፤ መደመር በአንድ ሀገር ውስጥ ያሉ የተለያዩ ሀብቶችን አሰባስቦ በመጠቀም ሀገርን መለወጥ እንደሚቻል የሚያሳይ እሳቤ ነው ይላሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአዲሱ የመደመር ትውልድ መፅሐፋቸው የትናንት፣ የዛሬ እና የነገ ትውልዶች ዕውቀት፣ ጉልበት፣ ጊዜና ጥበባቸውን ለጋራ ዓላማ ማዋል እንደሚገባቸው አሳይተዋል ነው ያሉት። የነገ ትውልድ ጥበብና አቅሙን አዳብሮ ሀገሩን በዓለም ላይ ከፍ ያለች ኢትዮጵያን ዕውን እንዲያደርግ መንገድ ጠቁሟል ብለዋል። የመደመር ትውልድ የዓለም አንድ አካል በመሆኑ ኢትዮጵያ ከተቀረው ዓለም ጋር ያላትን ትስስር እንዲያጎለብትና ሀብቱን አሟጦ እንዲጠቀም የአደራ መልዕክት ያስተላለፈ መፅሐፍ ነውም ብለዋል። ሌላኛው ባለሃብት ባህበሽ ኢንዳሪያ ብዝሃነት በሞላባት ዓለም ውስጥ ብዝሃ ጸጋን በአግባቡ ተጠቅሞ አካታች ዕድገትና ስልጣኔን ለማረጋገጥ የመደመር እሳቤ የወቅቱ መፍትሔ አመላካች መሆኑን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ'መደመር ትውልድ' መፅሐፋቸው ትውልዱ ለጋራ መዳረሻውን ውስጣዊ አቅሙን ይፈትሽ ዘንድ የዕውቀት ብልጭታ እንደሰጡ ጠቁመዋል። ባለሃብቶቹ አፍሪካዊያን ሀገር በቀል ጥበብ እንዳላቸው ጠቅሰው፤ የሀገራት መሪዎች ትውልድ ግንባታ በመጻፍና ሰርቶ በማሳየት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን አርዓያ ሊከተሉ እንደሚገባ ጠቁመዋል። የመደመር እሳቤ በራስ መተማመንና የማሳካት አቅም ያዳበረ ትውልድ በመገንባት የኢትዮጵያን፣ የአፍሪካ እና የዓለምን በርካታ ችግሮች መቅረፍ እንደሚቻልም አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ መሪነት ሚናዋ፣ ለመካከለኛው ምስራቅ ስትራቴጂክ ስፍራነቷ እንዲሁም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ላይ ከሚገኙ ሀገራት ተራ የተሰለፈች ሀገር መሆኗን ጠቅሰዋል። በመሆኑም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለም ያለው የመደመር ትውልድ ይበልጥ የበለጸገች፣ የታፈረች እና የተከበረች ኢትዮጵያን የመገንባት ማድረግ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
መንግስት የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ለሚያነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በቅንጅት ይሰራል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
Mar 25, 2023 201
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2015( ኢዜአ)፦መንግስት የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ለሚያነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በቅንጅት እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ ከጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ጋር በተለያዩ የልማት ጉዳዮች ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች የሰላም፣ የልማትና አስተዳደራዊ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ነዋሪዎቹ በጥያቄዎቻቸው በዞኑ የውሃ፣ የመንገድ፣ የጤናና የትምህርት ተቋማት ተደራሽነት ችግር መኖሩን ተናግረዋል። ይህም በዞኑ ነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና መፍጠሩን ገልጸዋል። በመሆኑም የጉራጌ ዞን ራሱን ችሎ በክልልነት በመደራጀት የልማት ጥያቄዎቹን ለመፍታት ያቀረበው ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ ይገባል የሚል ጥያቄ ተነስቷል። ነገር ግን የክልልነት ጥያቄን እንደሽፋን በመውሰድ በዞኑ አብረው በጋራ የኖሩ ህዝቦችን ለማጋጨት የሚሰሩ አካላት መኖራቸውን የጠቀሱት ነዋሪዎቹ፣ እነዚህ አካላት ተለይተው ለህግ እንዲያቀርቡም ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ በምላሻቸው በሁሉም አካባቢዎች በርካታ የመልማት ጥያቄዎች መኖራቸውን ገልፀው፤ መንግስት ያሉትን አቅሞች በማሰባሰብ ለጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ አኳያ መንግስት የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ላነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። ከህዝቡ ለተነሱት የልማት ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ረገድ ባለሃብቶችም የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። አስተዳደራዊ አደረጃጀት ለጥያቄዎች ሁሉ መልስ መስጫ መፍትሔ አለመሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ከአጎራባች ዞኖች ጋር ያላቸውን አብሮነት በማጠናከር በጋራ ለመልማት መስራት አለባቸው ብለዋል። የሚነሱ ጥያቄዎችን በሰለጠነና በሰከነ አግባብ መፍታት እንደሚገባም ጨምረው ገልጸዋል።
የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሰራዊት ለመገንባት የምታስገባቸውን ቴክኖሎጂዎች በአገር ውስጥ ለመተካት የጀመረውን ጥረት ማጠናከር አለበት -የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Mar 25, 2023 170
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2015 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲ ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሰራዊት ለመገንባት ከውጭ የምታስገባቸውን ቴክኖሎጂዎች በአገር ውስጥ ለመተካት የጀመረው ጥረት በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አሳሰቡ። ዩኒቨርሲቲው በምህንድስናና ጤና ሳይንስ የትምህርት መርሐ-ግብሮች በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ተማሪዎችን አስመርቋል። በምርቃት መርሐ-ግበሩ ላይ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፣ከፍተኛ መኮንኖችና የተለያዩ አገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል ። የአገር መከላከያ ሰራዊት የሚገጥሙ ፈተናዎችን በብቃት እያለፈ እንደሚገኝና ለዚህም እንደ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲ አይነት የትምህርት ተቋማት ትልቅ ሚና መጫወታቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ገልጸዋል። ዘመኑ የቴክኖሎጂ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂዎችን ማፍለቅ ላይ ርብርብ ማድረግ እንዳለበት ተናግረዋል። “መከላከያን የማዘመኑ ሂደት ቴክኖሎጂን ይፈልጋል ይህን ደግሞ ከውጭ በማስገባት ብቻ አይቀጥልም” ያሉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማጆር ሹሙ ዩኒቨርሲቲው ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባው ቴክኖሎጂ መተካት ላይ የጀመረውን ጥረት እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኮማንዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ከ75 በላይ መደበኛ መርሐግብሮች እንዳሉት ገልጸዋል። በነዚህ መርሐ-ግብሮች ተልዕኮውን በብቃት የሚወጣ ሰራዊት በማፍራት ላይ እንደሚገኝና በጥናትና በምርምር ዘርፍም ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማፍለቅ ዘመናዊ ሰራዊት እንዲገነባ እየሰራ ነው ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በሶስተኛ ዲግሪ መርሐግብር መስጠት መጀመሩን ገልጸው በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን ትምህርት ጥራት ለማሻሻል የስርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ነው ብርጋዴር ጀኔራሉ ያብራሩት። በሌላ በኩል ዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት አኳያ በግዳጅ ምክንያት ሕይወታቸውን ላጡ የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ልጆች ነጻ የትምህርት ዕድል እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በምርቃት መርሐ-ግብሩ ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሽልማት ተበርክቷል።
ፖለቲካ
አስፈጻሚ አካላት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ የኅብረተሰብ ጥያቄዎች ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Mar 27, 2023 57
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ አስፈጻሚ አካላት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ የኅብረተሰብ ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አሳሰቡ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመራጭ ኅብረተሰብ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል። ምክር ቤቱ በዓመት ሁለት ጊዜ ከመረጠው ሕዝብ ጋር ውይይት የሚያደርግ መሆኑ በውይይቱ ተገልጿል። ተመራጮቹ በቅርቡ ከመራጩ ሕዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት የልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሠላምና ደኅንነት እንዲሁም የኑሮ ውድነትን የተመለከቱ ጥያቄዎች ተነስተዋል፤ እነዚህም ጥያቄዎች ለሚመለከተው አስፈፃሚ አካላት ቀርበዋል። የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ መሠረት ኃይሌ በየምርጫ ክልሉ በነበረው ውይይት የተነሱ ጉዳዮችን በተመለከተ ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጓል። በዋናነት በውይይቶቹ የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ቀዳሚ ሲሆን ሌላኛው ከኑሮ ውድነት ጋር የተነሱ ጥያቄዎች አብዛኛውን ድርሻ መያዛቸውን ተናግረዋል። የኑሮ ውድነትና ሰው ሰራሽ የምርት እጥረት ኅብረተሰቡን እየፈተነ እንደሚገኝም ተመላክቷል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚንስትሩ ገብረመስቀል ጫላ የምርት እንቅስቃሴ ላይ ሲስተዋል የነበረው መስተጓጎል አሁን ላይ በተወሰዱ እርምጃዎች ምርቶች በሚፈለገው መጠን መንቀሳቀስ መጀመራቸውን ተናግረዋል። እንዲሁም በመላው አገሪቱ ባሉ የእሁድ ገበያዎች ሰፋ ያሉ የግብርና ምርቶች ቀርበው ለኅብረተሰቡ ተደራሽ መሆናቸውን ገልጸዋል። በሰው ሰራሽ የዋጋ ንረትና ሕገ-ወጥ ንግድ ላይ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ስለመሆኑ ተናግረዋል። ይህንን የኑሮ ውድነት ችግር መቅረፍ በአንድ ተቋም ብቻ የሚፈታ አለመሆኑን የገለጹት ሚንስትሩ ከተለያየ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሚተገበር የጋራ እቅድ ተዘጋጅቷል ብለዋል። ከኢኮኖሚ አሻጥሮች ጋር በተየያዘ ችግሮቹ እየተገመገሙ እርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁመዋል። በቀጣይ መንግሥት ቁጥጥር የሚያደርግባቸው ምርቶች የመለየት ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አመላክተዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አስፈጻሚ አካላት በአጭር ጊዜ መፈታት ያለባቸውን ችግሮች በቅድሚያ መፍታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። እንዲሁም ጊዜ የሚወስዱ ሥራዎች በአግባቡ ለኅብረተሰቡ ማስገንዘብ እንደሚገባ ተናግረዋል። አስፈጻሚዎች በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ የኅብረተረሰብ ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። እንዲሁም የፌደራልና የክልል አመራሮች እነዚህን ችግሮች ለመፍታት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
መንግስት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል-ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ
Mar 27, 2023 71
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ መንግስት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ገለጹ። የፍትሕ ስርዓቱን ብልሽቶች ማስተካከል አላማ ያደረገ የሶስት ዓመት የማሻሻያ ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በየካቲት ወር 2015 በምርጫ ክልላቸው በመገኘት ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። የምክር ቤቱ አባላት በውይይቶቹ ከሕብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን የያዘ ሪፖርት ዛሬ ለአስፈጻሚ አካላት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም በሁሉም አካባቢዎች በተደረጉ ውይይቶች የሰላም እና ጸጥታ ችግርን ሕብረተሰቡ ማንሳቱን ገልጸዋል። የዜጎች ተዘዋውሮ የመስራት መብት አለመከበር ጉዳይ መፍትሔ እንዲሰጠው እና የሕግ አስፈጻሚው አካል ሰላምን በሚያደፈርሱ አካላት ላይ እርምጃ በመውሰድ አስተማማኝ ሰላምን እንዲያሰፍንም አሳስበዋል። በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ከአገልግሎት አሰጣጥ አንጻር ያሉ ብልሹ አሰራሮች እንዲቀረፉ የምክር ቤት አባላቱ የሕዝብን ጥያቄ ዋቢ አድርገው አቅርበዋል። የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በተለያዩ አካባቢዎች ግጭት በመቀስቀስ፣ በመሳተፍና በማስተባበር የተጠረጠሩ በርካታ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በሕግ እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት በሃይማኖትና በብሔር ሽፋን ግጭት ለመቀስቀስ የሚሞክሩና የአገርን ሰላም የሚያውኩ አካላት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥና በሁሉም አካባቢዎች " ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን በትኩረት እየሰራ ነው" ብለዋል። ዶክተር ጌዲዮን አክለውም የፍርድ ቤት ጉዳዮችን ጨምሮ በፍትሕ ተቋማት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የፍትሕ ስርዓቱ ላይ ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተለይም አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሙስና ተግባር የሚፈጽሙ አካላት ላይ ቀጣይነት ያለው እርምጃ የመውሰድና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት። በሌላ በኩል የፍትህ ስርዓቱን ለማዘመን በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት የሚተገበር የማሻሻያ ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። ፍኖተ ካርታውን ወደስራ ለማስገባት እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ገልጸው የፍትሕ ስርዓቱ የሰው ኃይል ብቃት ላይም ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጄነራል ዘላለም መንግስቴ ባለፉት ስድስት ወራት ጠንካራ የሕግ ማስከበር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በዚህም በተለያዩ አካባቢዎች ግጭት በመቀስቀስ የሰላምና ፀጥታ ችግር የፈጠሩ ግለሰቦች ላይ እርምጃ መወሰዱን ጠቅሰዋል። የጸጥታ ስጋቶችን በአግባቡ የመምራት አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ መምጣቱን ገልጸው፤ የዜጎችን ሰላምና የሀገርን ልማት የሚያስተጓጉሉ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ላይ ጠንካራ እርምጃ ይወሰዳል ነው ያሉት ኮሚሽነር ጄነራሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት የመንግስትን የስድስት ወር ሪፖርት ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ
Mar 27, 2023 129
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት የመንግስትን የስድስት ወር አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ፡፡ ምክር ቤቱ ነገ በሚያካሂደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሚቀርበውን ሪፖርት ያዳምጣል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ የተለያዩ ወቅታዊና ሀገራዊ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡
ከመራጩ ህብረተሰብ በተነሱ ጉዳዩች ላይ ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው
Mar 27, 2023 98
አዲስ አበባ መጋቢት 18/ 2015 (ኢዜአ) በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመራጩ ህብረተሰብ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። ምክር ቤቱ በዓመት ሁለት ጊዜ ከመረጠው ሕዝብ ጋር ውይይት የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም በየካቲት ወር ባደረገው የሕዝብ ውክልና ስራ ከመራጩ ሕዝብ ጋር በተደረገ ውይይት የልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሠላም እና የኑሮ ውድነትን በተመለከተ ከመራጩ ሕዝብ የተነሱ ጥያቄዎችን ለሚመለከተው አስፈፃሚ አካላት መቅረቡ ተገልጿል። ይህንኑ በተመለከተ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ መሠረት ኃይሌ በየምርጫ ክልሉ የነበረው የውይይት ሂደት በተመለከተ ሪፖርት አቅርበው ውይይት እየተደረገ መሆኑን ከምክርቤቱ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
"በቀጣይ የብልጽግና ፓርቲ ዋናው የቤት ሥራ ነፃነትን በአግባቡ መጠቀም እና ማስተዳደር ላይ መሥራት ነው"-የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ
Mar 27, 2023 102
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ)፦ "በቀጣይ የብልጽግና ፓርቲ ዋናው የቤት ሥራ ነፃነትን በአግባቡ መጠቀም እና ማስተዳደር ላይ መሥራት ነው" ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ተናገሩ፡፡ "ድሎችን ማፅናት እና ፈተናዎችን መሻገር" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ወቅታዊ እና ታሪካዊ የአመራር ተልእኮ መድረክ በሀገራዊ የሰላም፣ የፀጥታ እና የልማት ጉዳዮች ላይ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው ውይይት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋናው ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ከተሳታፊ አመራሮች ለተነሡ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የኑሮ ውድነትን፣ የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ መንግሥታዊ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮችን በሚመለከት ብልጽግና ፓርቲ በትኩረት እንደሚሠራ አበክረው ገልጸዋል። ብልጽግና ፓርቲ አስቀድሞ የጀመራቸውን መርህን መሠረት ያደረጉ ተቋማዊ አሠራሮችን አጠናክሮ በማስቀጠል የፓርቲውን ሕዝባዊ ቅቡልነት ማሳደግ እና ጠንካራ መንግሥታዊ አቅም መፍጠር እንደሚገባም ጠቅሰዋል። ይህንንም ለማጠናከር አመራሩ የአመለካከት እና የተግባር አንድነቱን በማጠናከር በኅብረ ብሔራዊ አንድነት በተሰናሰለ ወጥ ሀገራዊ እሳቤ አቅም መሆን እንደሚገባው አንሥተዋል። የብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካዊ እሳቤዎች ኢትዮጵያዊ መሠረት ያላቸው እና የሀገራችንን እና የሕዝባችንን ችግር ፈቺዎች እንዲሆኑ ማድረግ፣ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ማሳደግ እና የሕዝቡን ፖለቲካዊ ሞጋችነት እና የልማት ተሳትፎ እንዲሁም ተጠቃሚነት በማሳደግ ቅቡልነትን ማሳገድ እንደሚገባም ማብራሪያ ሰጥተዋል። በአጠቃላይ ብልጽግና ፓርቲ መላ መዋቅራዊ አቅሙን ፈትሾ የሚታዩ የአመራር የአቅም ጉድለቶችን አርሞ፣ ውስጣዊ ብልሽቶችን አክሞ እና መርሕን መሠረት ባደረገ አግባብ ተግባራት በማሳለጥ የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ እና ዕድገት በማስቀጠል ሕዝባዊ ቅቡልነትን ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ እንደ ሀገር የመጣውን ነፃነት ከመጠቀም ጋር ሰፊ ክፍተት እንዳለ እና ነፃነትን ማክበር እና ማስከበር በሚመለከት ብልጽግና ፓርቲ የሚደራደርበት ጉዳይ እንዳልሆነ አሳስበዋል። እንደመሪ ፓርቲ ነፃነትን በአግባቡ መጠቀምና ማስተዳደር ላይ መሥራት እንደሚገባም አክለው ገልጸዋል። በተመሳሳይ ነፃነትን በፓርቲው ውስጥ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ እና የፓርቲው አመራር እና አባል ተገቢ ነፃነት ተጎናፅፎ ሐሳቡን ያለተፅዕኖ እያራመደ መቀጠል እንዳለበት በአፅንኦት አስቀምጠዋል። እንደ ሀገር የዴሞክራሲ፣ የፍትሕ እና የዳኝነት ተቋማት በነፃነት እና በገለልተኝነት ሥራቸውን አጠናክረው መሥራት እንደሚገባቸውም ለተሳታፊ አመራሮች ማንሣታቸውን ከፓርቲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የመደመር እሳቤ ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለምን መጻዒ ዘመን የተሻለ ለማድረግ ሁሉም ሊተገብረው የሚገባ መርህ ነው...የህንድ ባለሃብቶች
Mar 25, 2023 157
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2015 (ኢዜአ) የመደመር እሳቤ ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለምን መጻዒ ዘመን የተሻለ ለማድረግ ሁሉም ሊተገብረው የሚገባ መርህ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የሕንድ ባለሃብቶች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ የአስደናቂ ታሪክ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያ በመምራት ሂደት በተለይ የትውልድ ቀረጻ ላይ ማተኮራቸውን አድንቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን እና የትውልዱን መጻዒ ብሩህ ተስፋ የሚተልሙ መደመር፣ የመደመር መንገድ እና የመደመር ትውልድ የተሰኙ ሦስት መጻሕፍትን አበርክተዋል። ሦስቱም መጻሕፍት ማጠንጠኛ 'መደመር' ቢሆንም የመደመር እሳቤው ምንነት፣ ስለትግበራ መንገዱ እና ስለትውልዱ ትግበራ ወሰን በተለያዬ ዐውድ የሚያትቱ ናቸው። በቅርቡ የተመረቀው 'የመደመር ትውልድ' የተሰኘው ሶስተኛ መፅሓፋቸው የእንግሊዝኛ ቅጂ ለዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እና ለውጭ ባለሃብቶች በታደሙበት የማስተዋወቅ መድረክ ተካሂዷል። በኢትዮጵያ የሕንድ ባለሃብቶች ፎረም ምክትል ሰብሳቢ ራጂቭ ሻርማ እንዳሉት፤ መፅሐፉ የመደመር ትውልድ ከትናንት እንዲማርና የራሱን አቅሙን አሰባስቦ የተሻለች ሀገር እንዲገነባ መንገድ ያሳያል። የመደመር እሳቤ ዓለም አቀፋዊ መርሆን የሚያስተጋባ በመሆኑ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለተቀረው ዓለም የሚበጅ መሆኑንም እንዲሁ። አፍሪካውያን ከቀደመ ታሪካቸው እንዲማሩ፣ እርስ በርስ እንዲተዋወቁ ብሎም ወደ ፊት ጠንካራ አህጉር መገንባት የሚያስችል አቅማቸውን ወደ ተግባር እንዲለውጡ መንገድ የሚጠቁም መሆኑንም ተናግረዋል። የህንድ የቢዝነስ ፎረም አባል ካውሸል ሼድ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ጥንታዊትና አኩሪ ታሪክ ያላት እና መልከ ብዙ ውጣ ውረዶችን ያሳለፈች ሀገር መሆኗን አውስተዋል። የዘመኑ ትውልድም ከትናንት ታሪክ ቁም ነገሮችን ቀስሞ፤ በመደመር እሳቤ የተሻለ ነገን መገንባት እንደሚችል መመላከቱን ጠቁመዋል። ከቅደመ አያቶቻቸው ጀምሮ ቤተሰቦቻቸው ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ መኖራቸውን የሚናገሩት ሕንዳዊ ባለሀብት ሀርሺ ኮታሪ፤ መደመር በአንድ ሀገር ውስጥ ያሉ የተለያዩ ሀብቶችን አሰባስቦ በመጠቀም ሀገርን መለወጥ እንደሚቻል የሚያሳይ እሳቤ ነው ይላሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአዲሱ የመደመር ትውልድ መፅሐፋቸው የትናንት፣ የዛሬ እና የነገ ትውልዶች ዕውቀት፣ ጉልበት፣ ጊዜና ጥበባቸውን ለጋራ ዓላማ ማዋል እንደሚገባቸው አሳይተዋል ነው ያሉት። የነገ ትውልድ ጥበብና አቅሙን አዳብሮ ሀገሩን በዓለም ላይ ከፍ ያለች ኢትዮጵያን ዕውን እንዲያደርግ መንገድ ጠቁሟል ብለዋል። የመደመር ትውልድ የዓለም አንድ አካል በመሆኑ ኢትዮጵያ ከተቀረው ዓለም ጋር ያላትን ትስስር እንዲያጎለብትና ሀብቱን አሟጦ እንዲጠቀም የአደራ መልዕክት ያስተላለፈ መፅሐፍ ነውም ብለዋል። ሌላኛው ባለሃብት ባህበሽ ኢንዳሪያ ብዝሃነት በሞላባት ዓለም ውስጥ ብዝሃ ጸጋን በአግባቡ ተጠቅሞ አካታች ዕድገትና ስልጣኔን ለማረጋገጥ የመደመር እሳቤ የወቅቱ መፍትሔ አመላካች መሆኑን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ'መደመር ትውልድ' መፅሐፋቸው ትውልዱ ለጋራ መዳረሻውን ውስጣዊ አቅሙን ይፈትሽ ዘንድ የዕውቀት ብልጭታ እንደሰጡ ጠቁመዋል። ባለሃብቶቹ አፍሪካዊያን ሀገር በቀል ጥበብ እንዳላቸው ጠቅሰው፤ የሀገራት መሪዎች ትውልድ ግንባታ በመጻፍና ሰርቶ በማሳየት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን አርዓያ ሊከተሉ እንደሚገባ ጠቁመዋል። የመደመር እሳቤ በራስ መተማመንና የማሳካት አቅም ያዳበረ ትውልድ በመገንባት የኢትዮጵያን፣ የአፍሪካ እና የዓለምን በርካታ ችግሮች መቅረፍ እንደሚቻልም አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ መሪነት ሚናዋ፣ ለመካከለኛው ምስራቅ ስትራቴጂክ ስፍራነቷ እንዲሁም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ላይ ከሚገኙ ሀገራት ተራ የተሰለፈች ሀገር መሆኗን ጠቅሰዋል። በመሆኑም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለም ያለው የመደመር ትውልድ ይበልጥ የበለጸገች፣ የታፈረች እና የተከበረች ኢትዮጵያን የመገንባት ማድረግ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
መንግስት የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ለሚያነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በቅንጅት ይሰራል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
Mar 25, 2023 201
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2015( ኢዜአ)፦መንግስት የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ለሚያነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በቅንጅት እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ ከጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ጋር በተለያዩ የልማት ጉዳዮች ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች የሰላም፣ የልማትና አስተዳደራዊ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ነዋሪዎቹ በጥያቄዎቻቸው በዞኑ የውሃ፣ የመንገድ፣ የጤናና የትምህርት ተቋማት ተደራሽነት ችግር መኖሩን ተናግረዋል። ይህም በዞኑ ነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና መፍጠሩን ገልጸዋል። በመሆኑም የጉራጌ ዞን ራሱን ችሎ በክልልነት በመደራጀት የልማት ጥያቄዎቹን ለመፍታት ያቀረበው ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ ይገባል የሚል ጥያቄ ተነስቷል። ነገር ግን የክልልነት ጥያቄን እንደሽፋን በመውሰድ በዞኑ አብረው በጋራ የኖሩ ህዝቦችን ለማጋጨት የሚሰሩ አካላት መኖራቸውን የጠቀሱት ነዋሪዎቹ፣ እነዚህ አካላት ተለይተው ለህግ እንዲያቀርቡም ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ በምላሻቸው በሁሉም አካባቢዎች በርካታ የመልማት ጥያቄዎች መኖራቸውን ገልፀው፤ መንግስት ያሉትን አቅሞች በማሰባሰብ ለጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ አኳያ መንግስት የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ላነሷቸው የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። ከህዝቡ ለተነሱት የልማት ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ረገድ ባለሃብቶችም የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። አስተዳደራዊ አደረጃጀት ለጥያቄዎች ሁሉ መልስ መስጫ መፍትሔ አለመሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ከአጎራባች ዞኖች ጋር ያላቸውን አብሮነት በማጠናከር በጋራ ለመልማት መስራት አለባቸው ብለዋል። የሚነሱ ጥያቄዎችን በሰለጠነና በሰከነ አግባብ መፍታት እንደሚገባም ጨምረው ገልጸዋል።
የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሰራዊት ለመገንባት የምታስገባቸውን ቴክኖሎጂዎች በአገር ውስጥ ለመተካት የጀመረውን ጥረት ማጠናከር አለበት -የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Mar 25, 2023 170
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2015 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲ ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሰራዊት ለመገንባት ከውጭ የምታስገባቸውን ቴክኖሎጂዎች በአገር ውስጥ ለመተካት የጀመረው ጥረት በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አሳሰቡ። ዩኒቨርሲቲው በምህንድስናና ጤና ሳይንስ የትምህርት መርሐ-ግብሮች በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ተማሪዎችን አስመርቋል። በምርቃት መርሐ-ግበሩ ላይ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፣ከፍተኛ መኮንኖችና የተለያዩ አገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል ። የአገር መከላከያ ሰራዊት የሚገጥሙ ፈተናዎችን በብቃት እያለፈ እንደሚገኝና ለዚህም እንደ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲ አይነት የትምህርት ተቋማት ትልቅ ሚና መጫወታቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ገልጸዋል። ዘመኑ የቴክኖሎጂ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂዎችን ማፍለቅ ላይ ርብርብ ማድረግ እንዳለበት ተናግረዋል። “መከላከያን የማዘመኑ ሂደት ቴክኖሎጂን ይፈልጋል ይህን ደግሞ ከውጭ በማስገባት ብቻ አይቀጥልም” ያሉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማጆር ሹሙ ዩኒቨርሲቲው ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባው ቴክኖሎጂ መተካት ላይ የጀመረውን ጥረት እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኮማንዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ከ75 በላይ መደበኛ መርሐግብሮች እንዳሉት ገልጸዋል። በነዚህ መርሐ-ግብሮች ተልዕኮውን በብቃት የሚወጣ ሰራዊት በማፍራት ላይ እንደሚገኝና በጥናትና በምርምር ዘርፍም ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማፍለቅ ዘመናዊ ሰራዊት እንዲገነባ እየሰራ ነው ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በሶስተኛ ዲግሪ መርሐግብር መስጠት መጀመሩን ገልጸው በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን ትምህርት ጥራት ለማሻሻል የስርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ነው ብርጋዴር ጀኔራሉ ያብራሩት። በሌላ በኩል ዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት አኳያ በግዳጅ ምክንያት ሕይወታቸውን ላጡ የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ልጆች ነጻ የትምህርት ዕድል እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በምርቃት መርሐ-ግብሩ ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሽልማት ተበርክቷል።
ማህበራዊ
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለሕዝብ ጥያቄ መፍትሔን የሚያመነጭ አመራርን መፍጠር ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል - የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
Mar 27, 2023 52
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ) የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ በመረዳት ለህዝብ ጥያቄ መፍትሔን የሚያመነጭ አመራርን መፍጠር ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ሲል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳሰበ። በምክር ቤቱ የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአካዳሚውን የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ገምግሟል። በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የእቅድ፣ በጀትና ሪፎርም ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ጫኔ የተቋሙን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። በዚህም በግማሽ ዓመቱ ማዕከሉ በአዲስ መልክ መቋቋሙን ተከትሎ ተልዕኮውን በማሳካት ረገድ በርካታ ሥራዎችን አከናውኗል። በተለይም አጫጭር ሥልጠናዎችን መስጠት፣ የውጪ የትምህርት እድሎችን ማመቻቸት፣ የፖሊሲ ምርምሮችን ማካሄድና ተተኪ አመራሮችን ማብቃት ተጠቃሽ ናቸው። የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንን ጨምሮ ሥልጠናዎችን በበይነ-መረብ ለማካሄድ የሚያስችል ፕሮጀክት ተግባራዊ ማድረጉም እንዲሁ። ይሁን አንጂ ተቋሙ ከሚጠበቅበት ውጤት አኳያ በቂ ሥራዎች ተሰርተዋል ተብሎ እንደማይታመን አቶ ምትኩ አብራርተዋል። የቋሚ ኮሚቴው አባላት በበኩላቸው ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ ጥያቄና አስተያየት ሰንዝረዋል። በተለይም ከተቋሙ ስያሜ አኳያ ፓናፍሪካኒዝምን አጉልቶ በማሳየትና ተደራሽነቱን በማስፋት ረገድ ውስንነቶች እንዳሉ አንስተዋል። በፌዴራል፣ በክልልና የከተማ አስተዳደር አመራሮችን አቅም ከማሳደግ አኳያ ጎልተው የሚታዩ ሥራዎች አለመከናወናቸውንም የቋሚ ኮሚቴው አባላት ገልጸዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ በበኩላቸው ማዕከሉ በይፋ ሥራውን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ በርካታ ሥራዎችን ማከናወኑ አይዘነጋም። በተለይም ደግሞ የተቋሙን አሰራር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ያደረገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የእቅድ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ መሆኑ ደግሞ በትኩረት ሊታይና ሊፈተሽ እንደሚገባ ሰብሳቢው አንስተዋል። የሰው ሃይል አቅሙን ማደራጀት፣ የሥልጠና ብቃት ማረጋገጫ ተግባር ላይ መዋሉን ክትትል ማድረግና ወቅታዊና አስቸኳይ የሥልጠና ማንዋሎችን ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ ሌላኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን አብራርተዋል። በዋናነት የአገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገነዘብና ለሕዝብ ጥያቄ መፍትሄን የሚያመነጭ አመራርን መፍጠር ላይ አጽንዖት መሰጠት ያስፈልጋል ብለዋል። የአካዳሚው ፕሬዝዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ አካዳሚውን በአዲስ መልክ የማደራጀት ሥራው ጊዜ የወሰደ በመሆኑ በሚፈለገው ልክ እቅዱን ማሳካት አልተቻለም ብለዋል። ተደራሽነትን በማስፋት ረገድ በቂ ሥራዎች አለመሰራታቸውን ገልጸው በግማሽ ዓመቱ በሦስት የአፍሪካ አገራት ለሚገኙ የውጭ አገራት ሙያተኞች ሥልጠና ተሰጥቷል ነው ያሉት። የተልዕኮ መመሳሰል ካለባቸው ተቋማት ጋር በምን መልኩ መሥራት እንደሚያስፈልግ የሚደነግግ የሕግ ማዕቀፍ አለመኖሩም አካዳሚው ተልዕኮውን በአግባቡ እንዳይወጣ እንቅፋት ሆኖበታል ብለዋል። ያም ሆኖ አሁንም ቋሚ ኮሚቴው የሰጠውን አስተያየት መነሻ በማድረግ አካዳሚው የማስተካከያ ሥራዎችን በመሥራት ለላቀ ውጤት እንደሚተጋ ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
የአገር ውስጥ ጉዲፈቻ ስርዓትን በማጠናከር በችግር ውስጥ የሚገኙ ሕጻናትን ደህንነት መጠበቅ ይገባል - የበጎ አድራጎት ማህበራት
Mar 27, 2023 57
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ የአገር ውስጥ ጉዲፈቻ ስርዓትን በማጠናከር በችግር ውስጥ የሚገኙ ሕጻናትን ደህንነት መጠበቅ እንደሚገባ የበጎ አድራጎት ማህበራት አመለከቱ። የአዲስ አበባ የሴቶች ሕጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በችግር ውስጥ የሚገኙ ሕጻናትን በአገር ውስጥ ጉዲፈቻ ማሳደግ ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ዛሬ ከባለድርሻ አካላት ጋር አድርጓል። የበጎ አድራጎት ማኅበራት ተወካዮች በተለያዩ ምክንያት ችግር ላይ የወደቁ ሕጻናት የነገ አገር ተረካቢ በመሆናቸው እንክብካቤ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ገልጸዋል። በመሆኑም ሕጻናቱን የማሳደግ ሚና የተወሰኑ አካላት፣ የመንግሥትና የድርጅቶች ብቻ ሳይሆን የሁሉም ማኅበረሰብ አካላት የጋራ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል። በተለይም የአገር ወስጥ ጉዲፈቻን በማጠናከር አቅም ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች በጎዳና ላይ ኑሯቸውን ያደረጉ ሕጻናትን ማንሳት እንደሚጠቅባቸው አመልክተዋል። ለዚህም የግንዛቤ መፍጠር ስራዎች በስፋት ሊሲራ እንደሚገባ ነው የበጎ አድራጎት ማኅበራት ተወካዮች የተናገሩት። የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶችና ወጣቶች መመሪያ ኃላፊ ራምላ ከድር በበኩላቸው ለችግር የተጋለጡ ሕጻናትን መደገፍ ኃይማኖታዊ ተቀባይነት ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ማህበረሰቡ በተለያየ የችግር ደረጃ ላይ የሚገኙ ሕጻናትን መደገፍና መንከባከብ እንዳለበት ተናግረዋል። የአዲስ አበባ የሴቶች ሕጻናት ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሕጻናት መብት ደህንነት ማስጠበቅ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አናኒያ ያዕቆብ በበኩላቸው በችግር ውስጥ የሚገኙ ሕጻናትን በአገር ውስጥ ጉዲፈቻ ማሳደግ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መፍጠር ስራ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል። በርካታ ሕጻናት በግለሰብ የጉዲፈቻ ስርዓት ውስጥ ተሳታፊ መሆናቸውን ጠቁመው የሕጻናቱን ደኅንነት ማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች ጎን ለጎን እየተከናወኑ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ከ2007 እስከ 2014ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ 1ሺህ 252 ሕጻናት በግለሰብ ደረጃ በጉዲፈቻ እያደጉ መሆኑን ከከተማው የሴቶች ሕጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ቢሮው በማህበረሰብ አቀፍ የሕጻናት ድጋፍና ክብካቤ፣ መልሶ የማቀላቀልና ከማህበረሰቡ ጋር ማዋሃድ፣ የአደራ ቤተሰብ፣ የአገር ውስጥ ጉዲፈቻና የማሳደጊያ አማራጮችን በመጠቀም ችግር ውስጥ ያሉ ሕጻናትን እየደገፈ እንደሚገኝ ገልጿል።
መንግስት ሁሉም ስፖርቶች ከአበረታች ቅመሞች የፀዱ ሆነው እንዲከናወኑ ጽኑ የሆነ አቋም አለው--ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
Mar 27, 2023 79
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦መንግስት ሁሉም ስፖርቶች ከአበረታች ቅመሞች ነጻ ሆነው እንዲከናወኑ ጽኑ አቋም እንዳለው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ። የዓለም ፀረ-አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ (ዋዳ) በበኩሉ ኢትዮጵያ አበረታች ቅመሞችን በመከላከልና በመቆጣጠር እያከናወነች ያለውን ተግባር አድንቋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከኤጀንሲው ፕሬዝዳንት ዊቶልድ ባንካ ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። አቶ ደመቀ ስፖርት በአገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ከሚጠቅሙ የዲፕሎማሲ መሳሪያዎች አንዱ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ የታላላቅ አትሌቶች መገኛ መሆኗን ገልጸው መንግስት ዋዳን ጨምሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር አበረታች ቅመሞችን ለመዋጋት በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል። መንግስት ሁሉም ስፖርቶች ከአበረታች ቅመሞች የፀዱና ነጻ ሆነው እንዲከናወኑ ጽኑ የሆነ አቋም እንዳለውም ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የተቀናጀ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ስርዓትን በመዘርጋት በሁሉም ስፖርቶች አበረታች ቅመሞችን ለመዋጋት እየተከተለቻቸው ያሉ የተለያዩ አማራጮች ውጤታማ መሆናቸውን አቶ ደመቀ አስረድተዋል። የዓለም ፀረ-አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ (ዋዳ) ፕሬዝዳንት ዊቶልድ ባንካ ኢትዮጵያ አበረታች ቅመሞችን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ እያከናወነች ያለውን ተግባር አድንቀዋል። ዋዳ ኢትዮጵያ አበረታች ቅመሞችን ለመዋጋት ያላትን ተቋማዊ አቅም ለመገንባት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ዋና መቀመጫውን በካናዳ ሞንትሪያል ያደረገው የዓለም ፀረ-አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ (ዋዳ) የተቋቋመው እ.አ.አ ሕዳር 10/1999 ነው። ኤጀንሲው በስፖርታዊ ውድድሮች አበረታች ቅመሞች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የመከታተል፣ የማስተባበርና ግንዛቤ የመፍጠር ስራን ያከናውናል።
በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የአይን ሞራ ግርዶሽ የነፃ ህክምና መስጠት ተጀመረ
Mar 27, 2023 54
ሰቆጣ፣ መጋቢት 18 ቀን 2015 (ኢዜአ) በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የአይን ሞራ ግርዶሽና ተያያዥ ችግሮች ላለባቸው አንድ ሺህ ሰዎች ነፃ ህክምና መስጠት መጀመሩን የአስተዳደሩ ጤና መምሪያ አስታወቀ። የብሄረሰብ አስተዳደሩ ጤና መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ እንዳሉት፤ በዓይን ሞራ ግርዶሽና ትራኮማ ችግር ለአይነ ስውርነት የሚዳረጉ ሰዎችን ለመታደግ የሚያስችል ህክምና ተጀምሯል። ከዚህ ቀደም ህክምናውን በቅርበት መስጠት ባለመቻሉ ችግሩ ያጋጠማቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ህክምናውን ለማግኘት ደሴና ባህር ዳር ከተሞች ድረስ ለመጓዝ ይገደዱ እንደነበር አስታውሰዋል። ችግሩን በቅርበት ለመፍታት ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ የመጡ 10 የሃኪሞች ቡድን የአይን ሞራ ግርዶሽና ተያያዥ ችግር ያለባቸውን ሰዎች በመለየትና ህክምና መስጠት መጀመሩን ተናግረዋል። የሃኪሞች ቡድኑ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ስድስት ቀናት አንድ ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች ህክምናውን እንደሚሰጥ ገልጸው፤ ህክምናው በቅርበት መሰጠት መቻሉ የታካሚዎችን ድካምና ወጪ ማስቀረቱን ተናግረዋል። ችግሩ ያለባቸውን ወገኖች ልየታ በማድረግ በሰቆጣ ተፈራ ሃይሉ መታሰቢያ ሆስፒታል ህክምና እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ አቶ መሰረት ምህረቱ ካለፈው ዓመት ጀምሮ የእይታ መጋረድ ችግር እንዳጋጠማቸው ለኢዜአ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የነፃ የዓይን ህክምና መስጠት መጀመሩ አቅመ ደካሞችን ድካምና እንግልት እንዲሁም የገንዘብ ወጪን የሚያስቀር መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ወንድሙ ታለፈ በበኩላቸው የነፃ የአይን ህክምናው ለበርካታ ዓመታት በዓይን ህመም የሚሰቃዩ ሰዎችን ተስፋና እፎይታን የሚሰጥ ነው ብለዋል። ለሁለት ዓመታት ያክል በዓይኔ ላይ በደረሰብኝ ህመም ምክንያት ለእይታና ለሌሎች ችግሮች አጋልጦኛል ያሉት አቶ ወንድሙ፤ በሚሰጠው ህክምና መፍትሄ እንደሚያገኙ ተስፋ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
ኢኮኖሚ
ከህብረተሰቡ ለሚነሱ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች በፍትሃዊነት አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው-የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ
Mar 27, 2023 46
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ) ከህብረተሰቡ ለሚነሱ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች በፍትሃዊነት አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኣባላት ከመራጭ ኅብረተሰብ የተነሱ ጥያቄዎችን በሚመለከት ከአስፈፃሚ አካላት ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን፤ የመንገድ፣ የውሃና የመብራት ተደራሽነት ጥያቄዎች ከኀብረተሰቡ መነሳታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይም ከመብራት እና ከቴሌኮም አገልግሎት መቆራረጥ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ ምላሽ እንደሚሻም ተመላክቷል። የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ አለመጠናቀቅ ህብረተሰቡን አሁንም ለቅሬታ የዳረጉ ጉዳዮች መሆናቸው ተነስቷል። የፕላን እና ልማት ሚንስትሯ ዶክተር ፍጹም አሰፋ በዚሁ ወቅት መሰረተ ልማትን በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረው ጦርነት በመሰረተ ልማት አውታሮች ላይ ጉዳት ማድረሱንና ፕሮጀክቶች እንዲጓተቱ ማድረጉንም ጠቁመዋል፡፡ በቀጣይ መንግስት ይህን ለማስተካከል በትኩረት እየሰራ መሆኑን በማንሳት፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በበኩላቸው በመብራት መሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች አሁንም ለአገልግሎቱ መቆራረጥ ምክንያት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን የማዘመና የተባላሹ መስመሮች በመጠገን ተደራሽ እንዲሆን እየሰራ ነው ብለዋል። በቀጣይም ከህብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩም በአገር አቀፍ ደረጃ የቴሌኮም ኔትወርክ አቅምን የማሳደግ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። ኩባንያው የቴሌኮም ተደራሽነትን ለማስፋትና የአገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ የመሰረተ ልማት ማስፋፋትን ጨምሮ የጥገና ስራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ አብራርተውል፡፡ በበጀት ዓመቱ በአገር አቀፍ ደረጃ 320 የመንገድ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን ናቸው። ለግንባታ የሚሆኑ ጥሬ እቃዎች ዋጋ መናር አሁንም ዘርፉን እየፈተነው መሆኑን ጠቅሰው፤ ችግሩን በመቋቋም የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በጋምቤላ ክልል የውሃና የመሬት ሀብትን ለልማት በማዋል የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥ እየተሰራ ነው--የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ
Mar 27, 2023 64
ጋምቤላ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰፊ የውሃና የመሬት ሀብት ለልማት በማዋል የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ አስታወቀ። በአርብቶ አደር ፖሊሲና የማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ላይ የክልሉ አመራሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተወያይተዋል። የቢሮው ኃላፊ አቶ ኮንግ ጆክ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት መንግስት በአርብቶ አደር አካባቢዎች ያለውን የተፈጥሮ ሀብት ግምት ውስጥ ያስገባ ፖሊሲና ስትራቴጂ በመቅርጽ ወደ ሥራ መግባቱን ገልጸዋል። የተቀረጸው ፖሊሲ የክልሉን አርሶና አርብቶ አደሮች ኑሮ የሚለውጥና የሚያሻሽል በመሆኑ ለአመራሩ በቂ ግንዛቤ በማስያዝ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ ፒን ኡጁሉ በበኩላቸው፣ በክልሉ ያለውን ሰፊ የመሬትና የውሃ ሀብት በማልማት የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ በግንባታ ሂደትና ተገንብተው መጠነኛ ችግር ያለበችውን ስምንት የመስኖ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ በማስገባት ተጠቀሚ ለማድርግ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህም በተጨማሪ በክልሉ ከ30ሺህ ሄከታር በላይ መሬት ማልማት የሚያስችሉ 12 ከፍተኛና መካከለኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ጥናት እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል። ጥናቱ እየተካሄደ ያለው በክልሉ ቢሮ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስቴር ትብብር መሆኑን ገልጸዋል። የመስኖ ግብርና ልማቱ በቴክኖሎጂ እንዲደገፍ ሚኒስቴሩ 36 የእርሻ ትራክተሮችን ድጋፍ ማድረጉን ምክትል ቢሮ ኃላፊው አስታውቀዋል። በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስቴር የቆላማ አካባቢ ምርምር ዴስክ ኃላፊ አቶ አሸብር ደምለው በበኩላቸው መስሪያ ቤቱ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የአርብቶ አደሩንና ቆላማ አካባቢዎችን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተከናወኑት ሥራዎች በቂ ናቸው ባይባልም አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቁመው በቀጣይም ሚኒስቴሩ የጀመረውን ድጋፍ የማስተባበር ሥራ አጠናከሮ ይቀጥላል ብለዋል። በቢሮውና በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ትብብር በተዘጋጀው የአርብቶ አደር ፖሊሲና የማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ውይይት ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳተፈዋል።
የዋጋ ንረቱን በዘላቂነት ለመቅረፍ የግብርና ምርቶች በስፋት ወደ ከተማው እየገባ ነው-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
Mar 27, 2023 52
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዋጋ ንረቱን በዘላቂነት ለመቅረፍ ከክልሎች ጋር ባደረገው የገበያ ትስስር የግብርና ምርቶች በስፋት ወደ ከተማዋ እየገቡ እንደሚገኙ ተገለጸ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከክልሎች ጋር እያደረገ ባለው የገበያ ትስስር በዛሬው ዕለት ከኦሮሚያ ክልል ከ42 ሺህ ኩንታል በላይ የግብርና ምርት መግባቱ ተገልጿል። የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ ዛሬ ወደ ከተማዋ ከገቡት የግብርና ምርቶች በተጨማሪ በቅርቡ ከ40 እስከ 50ሺህ ኩንታል ልዩ ልዩ የግብርና ምርቶች በቀጣይ ቀናት ወደ ከተማዋ ይገባሉ ብለዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ የዋጋ ንረቱን በዘላቂነት ለመቅረፍ ከክልሎች ጋር ባደረገው የገበያ ትስስር የግብርና ምርቶች በሚፈለገው ደረጃና በስፋት ወደ ከተማዋ እየገቡ እንደሚገኙ ገልፀዋል። የግብርና ምርቶችን በመሰወር የገበያ አለመረጋጋት የሚፈጥሩ ነጋዴዎችን ህብረተሰቡ እንዲጠቁም ጥሪ ማቅረባቸውን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በትውልዱ ላይ ያሳደረውን የይቻላል መንፈስ በማጠናከር በተባበረ ክንድ ግንባታውን ማጠናቀቅ እንደሚገባ ተገለጸ
Mar 27, 2023 51
ሚዛን አማን መጋቢት18/2015(ኢዜአ)፦ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የይቻላል መንፈስን የፈጠረና ለመጪው ትውልድ የሚተላለፍ ታሪካዊ ቅርስ በመሆኑ ህብረተሰቡ ለግድቡ ግንባታ ድጋፉን እንዲያጠናክር ጥሪ ቀረበ። ለግድቡ ግንባታ ገቢ ማሰባሰብን ዓላማ ያደረገ ሁለተኛ ዙር የሕዳሴው ግድብ ጉዞ ወደ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ተካሂዷል። ከጋምቤላ ክልል ተነስቶ ወደ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለመጣው የጉዞ ልዑክ አባላትም ዛሬ በቤንች ሸኮ ዞን አቀባበል የተደረገ ሲሆን በሚዛን አማን ከተማም ቦንድ የመሸጥ መርሃ ግብር ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ተወካይ አቶ መኮንን መንገሻ እንዳሉት፣ ግድቡ በኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንድ፣ ጉልበትና ገንዘብ እየተገነባ አሁን ያለበት ደረጃ ላይ ደርሷል። "ፕሮጀክቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ የተለያዩ የውጭና የውስጥ ፈተናዎች ቢገጥሙም በኢትዮጵያዊያን ህብረት ፈተናዎችን በማለፍ ዛሬ ላይ ደርሷል" ብለዋል። ፕሮጀክቱ የይቻላል መንፈስን የፈጠረና ለመጪው ትውልድ ጭምር የሚተላለፍ ታሪካዊ ቅርስ በመሆኑ ህብረተሰቡ አስከ መጨረሻው ድጋፉን እንዲያጠናክር አቶ መኮንን ጥሪ አቅርበዋል። ተወካዩ እንዳሉት የግድቡ ግንባታ ሥራ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት ዓመታት ከ17 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ከኢትዮጵያውያን ተሰባስቧል። ግድቡ ያለ ልዩነት ኢትዮጵያዊያንን ያስተሳሰረ የጋራ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመው፣ የዛሬው ትውልድ በቀጣይ የሚዘከርበት ተግባር መሆኑንም አመልክተዋል። አቶ መኮንን እንዳሉት የግድቡን ግንባታ ለማጠናቀቅ የቦንድ ሽያጭ ሳምንት በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በመካሄድ ላይ ይገኛል። ከቦንድ ግዥ ባለፈ ኢትዮጵያዊያን 8100 ላይ "A" ብለው በመላክ ድጋፋቸውን እንዲያጠናከሩ ጠይቀዋል። የሕዳሴው ግድብ ጉዞ ዋና አስተባባሪ አቶ አምሃ ዓለሙ በበኩላቸው ጉዞው ለግድቡ የሚያስፈልግ ገቢ ለማሰባሰብ የሚያስችል ንቅናቄ የመፍጠር ዓላማ እንዳለውም ተናግረዋል። በዚህኛው ዙር የሕዳሴ ጉዞም 200 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማሰባሰብ ግብ ተቀምጦ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። በየአካባቢው ከፍተኛ የሕብረተሰብ ተሳትፎ መኖሩን ገልጸው፣ ገቢ የማሰባሰብ ንቅናቄው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለአንድ ሳምንት እንደሚቆይ ገልጸዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቀበሌ መንገሻ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ የግድቡ ግንባታ ሥራ ብዙ ጫናዎችን ተሻግሮ አሁን ለደረሰበት ደረጃ መብቃቱ መላው ኢትዮጵያዊንን የሚያኮራ ነው። የዞኑ ህዝብ ቀሪው የግንባታ ሥራ እንዲጠናቀቅ ቀደም ሲል ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ እንዲያጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በማደግ ላይ ያሉ አገሮች ለአካታች ዲጂታል ኢኮኖሚ ትግበራ ትኩረት ሰጥተው ካልሰሩ እኤአ በ2025 ከ1 ትሪሊየን ዶላር በላይ ገቢ ሊያጡ ይችላሉ- ተመድ
Mar 27, 2023 69
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ በማደግ ላይ ያሉ አገሮች ለአካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ትግበራ ትኩረት ሰጥተው ካልሰሩ እኤአ በ2025 ከአገር ውስጥ ዓመታዊ ምርታቸው ከ1 ትሪሊየን ዶላር በላይ ገቢ ሊያጡ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ "የፈጠራና ቴክኖሎጂ ለፆታ እኩልነት" በሚል መሪ ሃሳብ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ውይይት አካሂዷል። የድርጅቱ የሰብአዊ ጉዳዮች የኢትዮጵያ አስተባባሪ ዶክተር ካትሪን ሶዚ፤ የዲጂታል ዘመን ሥራዎችን ቀላል በማድረግ በተለይም ሴቶችና ህፃናትን ተጠቃሚ ሊያደርጉ የሚችሉ በርካታ ዕድሎችን ይዞ መጥቷል ብለዋል። በዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም ከኢንተርኔት ተደራሽነት ውጭ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ተደራሽነቱን ማስፋት አስፈላጊ ነው ሲሉ ገልጸዋል። አካታች የዲጂታል ስትራቴጂ ተግባራዊ አለማድረግ በማኅበራዊና የምጣኔ ሃብት እድገት ላይ ተጽዕኖው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፤ አገሮች በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ነው ያሉት። አፍሪካን ጨምሮ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ባለፉት አሥርት ዓመታት ለአካታች ኢንተርኔት ትኩረት ባለመስጠታቸው ከዓመታዊ የአገር ውስጥ ምርታቸው 1 ትሪሊየን ዶላር ማጣታቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም መንግሥታት ክፍተቱን ለመሙላት ለአካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ትኩረት ሰጥተው ካልሰሩ እ.ኤ.አ በ2025 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ዶላር ሊያጡ ይችላሉ ሲሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል። የክህሎትና እውቀት ክፍተት፣ የኢንተርኔት ዋጋ አቅምን ያገናዘበ አለመሆን፣ ፆታዊ ትንኮሳ፣ የመጠቀሚያ መሳሪያዎች እጥረት የዘርፉ ፈተናዎች መሆናቸውን ዶክተር ካትሪን ገልጸዋል። በ2025 ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታዋን የተሳካ ለማድረግ ስትራቴጂ ቀርፃ እየሰራች መሆኑን ጠቅሰው፤ ዕቅዱ የተሳካ እንዲሆን አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ፤ በኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፉ እየተወሰዱ ያሉ የለውጥ ሥራዎችና የተገኙ ውጤቶችን አብራርተዋል። በ2025 ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሁሉንም ባሳተፈ መልኩ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የሴቶችን የዲጂታል አቅም ለማሳደግ ክህሎትና እውቀት ላይ ትኩረት ያደረጉ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በሴቶችና በወንዶች መካከል ያለውን የዲጂታል ተጠቃሚነት ዕድልና ክህሎት ልዩነት ለማጥበብ እንደ አገር ጥናት እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል። በቀጣይም መሰል ተግባራት ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ጠቅሰው፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ እውን ይሆናል ብለዋል።
አካታች የዲጂታል ምጣኔ ሀብትን እውን ለማድረግ እውቀትና ክህሎትን ማሳደግ ላይ እየተሰራ ነው
Mar 27, 2023 88
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ አካታች የዲጂታል ምጣኔ ሀብትን እውን ለማድረግ እውቀትና ክህሎት ላይ ትኩረት አድርጋ እየሰራች መሆኑ ተገለጸ። አለም አቀፍ የሴቶች ቀን በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የሴቶችን የዲጂታል ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት በማድረግ ተከብሯል። በዚሁ ጊዜ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ በኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፉ እየተወሰዱ ያሉ ሪፎርሞችን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ተግባራዊ እያደረገች ባለችው ዲጂታል 2025 መርሃ-ግብር ሴቶች ቴክኖሎጂን በሚፈለገው ደረጃ እንዳይጠቀሙ ካደረጉ ችግሮች ውስጥ የዲጂታል ክህሎትና እውቀት ማነስ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የሴቶችን የዲጂታል አቅም ለማሳደግ ክህሎትና እውቀት ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባራትን በማከናወን አካታች ምጣኔ ሀብትን ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም በሴቶችና በወንዶች መካከል የዲጂታል ዕውቀት ልዩነትን ለማጥበብ እንደ ሀገር ጥናት እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል። በቀጣይ በጥናቱ ግኝት መሰረት እስትራቴጂ በመቅረጽ ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ኢትዮጵያ በዲጂታል 2025 የያዘቻቸውን እቅዶች ለማሳካት ድጋፍ እንደሚያደርግ በመድረኩ ላይ የተገኙት የድርጅቱ ተወካይ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ አካታች ዲጅታል መርሃ ግብሮችን ባለመተግበር በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች ከኢንተርኔት ተደራሽነት ውጭ እንደሆኑ በመድረኩ ተነግሯል።
የቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት ለኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚቀጥል ገለጸ
Mar 25, 2023 171
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2015(ኢዜአ)፦ የቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት ለኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ እያደረገ ያለውን ድጋፍ እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ፒ.ኤች.ዲ.) ከቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት ዋና ሊቀመንበር ሰር ቶኒ ብሌር ጋር በጽህፈት ቤታቸው ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለው ትብብርና በቀጣይ ለመስራት ባቀዷቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ማህበራዊ ትስስር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። የቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 (ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን) ስትራቴጂ ከዝግጅት ወቅት አንስቶ እስከ ማስፈጸም ሂደት በቴክኒክ(ባለሙያ)፣በኢ-ሰርቪስ ትግበራ ላይ ጥናት በማድረግ፣የማስፈጸም አቅም እንዲሁም የአደረጃጀትና የስራ ሂደትን ለማሻሻል የሚያስችል ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱ ተገልጿል። ኢንስቲትዩቱ ከዲጂታል መሰረተ ልማት አኳያ በዳታ ሴንተር፣በኢንተርኔት ተደራሽነት፣ በክላውድና በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ላይ በቀጣይ ሊያደርገው በሚችለው ድጋፍ ውይይት መደረጉ ተመላክቷል። በሌላ በኩል የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሄ ዘሚካኤል ለሰር ቶኒ ብሌር የዲጂታል መታወቂያን አገልግሎቶች አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዳይሬክተሩ ኢንስቲትዩቱ ለአገልግሎቱ የሚያደርገውን ድጋፍ እና ከመሰረተ ልማት ጋር ያሉ ተግዳሮቶች ላይም ገለጻ አድርገዋል። የ69 ዓመቱ የእንግሊዝ የቀድሞ ፖለቲከኛ አገሪቷን ከእ.አ.አ 1997 እስከ 2007 በጠቅላይ ሚኒስትርነት አገልግለዋል።
ኢትዮ-ቴሌኮም በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የመሪነቱን ሚና እየተወጣ ነው-ፍሬህይወት ታምሩ
Mar 24, 2023 177
አዲስ አበባ መጋቢት 15/2015 (ኢዜአ) ኢትዮ- ቴሌኮም በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ የመሪነቱን ሚና እየተወጣ መሆኑን የኢትዮ- ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ-ቴሌኮም በአዲስ መልክ ያበለጸገውን ቴሌ ብር "ሱፐር አፕ" የሞባይል መተግበሪያ ይፋ አድርጓል። መተግበሪያው ደንበኞች የዕለት ተዕለት ተግባራቸውን ለማቅለልና በቴክኖሎጂ የታገዘ የንግድ ስራዎችን ለማሳለጥ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። በአንድ ጊዜ ፈርጀ ብዙ የዲጂታል ግብይት አገልግሎቶችን እንዲያገኙና ለማንኛውም የግዢ ሂደት እንዲጠቀሙ የሚያስችል መተግበሪያ መሆኑም ተመላክቷል። ይህ አዲሱ መተግበሪያ አሁን በስራ ላይ ካለው የቴሌብር መተግበሪያ ጋር ተያይዞ የሚታዩ የአፈጻጸም፣ የሴኩሪቲ ሲስተም፣ የስልክ ዳታ የመያዝ አቅም ውስንነትንና ሌሎች የመሳሰሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል መሆኑም ተነግሯል። እንዲሁም የማይ- ኢትዮ- ቴል መተግበሪያንና ሌሎች መተግበሪያዎችን በአንድ በማካተት የተቀናጀ፣ ብቁ እንዲሁም አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት የሚያስችል ነው ተብሏል። የኢትዮ -ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኩባንያው አገልግሎቱን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ ይገኛል። የዲጂታል ኢኮኖሚን እውን የማድረግ ሥራን አጠናክሮ በመቀጠል ኢትዮ-ቴሌኮም በዘርፉ የመሪነት ሚናውን እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም በቴክኖሎጂ መታገዝ ወሳኝ መሆኑን ተናግረው፤ በዛሬው ዕለት ይፋ የሆነውም መተግበሪያ ይህንኑ እንደሚያጎለብት ተናግረዋል። ሌላኛው የስማርት ስልክ አጠቃቀም መሆኑን ገልጸው አሁን ላይ በኔትወርክ ላይ ከተመዘገቡት 81ሚሊየን ቀፎዎች ውስጥ 46 በመቶ የሚሆኑት የስማርት ቀፎዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረገው መተግበሪያ ቴሌ ብር ሱፐር አፕ ለተለያዩ አገልግሎት የምንጠቀምባቸው አፕሊኬሽኖችን በአንድ መተግበሪያ ላይ ሁሉንም መጠቀም የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ጊዜንና ወጭን በመቆጠብ ረገድ መተግበሪያው ትልቅ ሚና እንዳለውም ጠቁመዋል።
ስፖርት
“በዛሬው ጨዋታ ጥሩ ውጤት ይዞ መውጣት የሚያስችል የስነ-ልቦና ዝግጅት አድርገናል”-አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
Mar 27, 2023 78
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ)፦ በኮትዲቯር አስተናጋጅነት በሚካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ከጊኒ ጋር ሁለተኛውን የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ዛሬ ታደርጋለች። የሁለቱ አገራት ጨዋታ በሞሮኮ ራባት በሚገኘውና 45ሺህ ተመልካች በሚያስተናግደው ልዑል ሙላይ አብደላ ስታዲየም ከምሽቱ 4 ሰዓት ይካሄዳል። በምድብ አራት የሚገኙት ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም ባደረጉት ጨዋታ ጊኒ 2 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል። የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የዛሬውን ጨዋታ አስመልክቶ በሰጠው አስተያያት “ከመጀመሪያው ጨዋታ በኋላ አብዛኛው ትኩረት የነበረው ተጫዋቾቹን ከሽንፈቱ በኋላ ከነበረው ስሜት ወጥተው ለዛሬው ጨዋታ በስነ ልቦናና አዕምሮ ዝግጁ እንዲሆኑ ማድረግ ነው” ሲል ገልጿል። በጊኒ ለተወሰደብን ብልጫ መልስ ለመስጠትና ጨዋታውን ለመቆጣጠር ከአዕምሮ ዝግጁነት ይልቅ አካላዊ ፍልሚያና ስሜታዊነት ላይ ትኩረት ማድረጋችን ለነሱ ይበልጥ እንዲመቻቸው ማድረጉን ተናግሯል። ይህም ተጫዋቾቹ ከጨዋታው ውጤት ለማግኘት ከነበራቸው ከፍተኛ ጉጉትና በአዕምሯቸው ስለው የገቡትና ሜዳ ላይ የነበረው ነባራዊ እውነት የተለያዩ ከመሆናቸው እንደሚመነጭ አመልክቷል። “በታዩት ክፍተቶች ላይ ውይይት መደረጉንና ከዛሬው ጨዋታ ጥሩ ውጤት ይዞ ለመውጣት ዝግጅታችንን ጨርሰናል” ነው ያለው አሰልጣኝ ውበቱ። የአማካይ ተጫዋቹ ጋቶች ፓኖም በሁለት ቢጫ ካርድ ምክንያት በቅጣት በዛሬው ጨዋታ የማይሰለፍ ሲሆን የተከላካይ መስመር ተጫዋቹ ምኞት ደበበ ከአንድ ጨዋታ ቅጣት መልስ ለዛሬው ጨዋታ ዝግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የሁለቱን ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ የ36 ዓመቱ ቻዳዊ ኢንተርናሽናል ዳኛ አልሀጂ አላው ማህማት በዋና ዳኝነት ይመሩታል። ኢትዮጵያ በምትገኝበት ምድብ አራት ማላዊ ከግብጽ ነገ ከቀኑ 10 ሰዓት በቢንጉ ናሽናል ስታዲየም ይጫወታሉ። በምድብ አራት ግብጽ እና ጊኒ በተመሳሳይ ስድስት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው አንደኛና ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል። ኢትዮጵያ በሶስት ነጥብ የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች። ዋልያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫ የመሳተፍ እድላቸውን ለማስፋት የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ ይጠበቅባቸዋል።
ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድርን አትሌት መዲና ኢሳ በአንደኝነት አጠናቀቀች
Mar 26, 2023 120
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድርን አትሌት መዲና ኢሳ በአንደኝነት አጠናቀቀች። አትሌት መዲና ኢሳ በመሪነት በማጠናቀቋ የ70ሺህ ብር ተሸላሚ ስትሆን በተጨማሪም በውድድሩ አዲስ ክብረ-ወሰን በማስመዝገቧ የ50ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶላታል። በውድድሩ አትሌት ፅጌ ገብረ ሰላማ 2ኛ እንዲሁም አትሌት መልክናት ውዱ 3ኛ ደረጃን ይዘው በማጠናቀቃቸው እንደቅደም ተከተላቸው የ45ሺህ ብር እና የ30ሺህ ብር ተሸላሚ ሆነዋል። በውድድሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረ ሥላሴ፣ አትሌት መሰረት ደፋር፣ አትሌት ለተሰንበት ግደይን ጨምሮ የተለያዩ አትሌቶችና እንግዶች ተገኝተዋል። የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎሜትር ሩጫ ”ቦታዬ፤ መብቴ፤ ድምፄ” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው በዚህ ውድድር አትሌቶች፣ 15 ሺህ የጤና ሯጮች፤ እንዲሁም አምባሳደሮች እየተሳተፉ ነው።
20ኛው የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ነው
Mar 26, 2023 111
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው 20ኛው የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ነው። ውድድሩ መነሻና መድረሻውን አዲስ አበባ ቦሌ አትላስ አካባቢ አድርጎ እየተካሄደ ነው። የዘንድሮው ዓመት ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ”ቦታዬ፤ መብቴ፤ ድምፄ” በሚል መሪ ቃል ነው የሚካሄደው። በዚህ ውድድር ላይ በአትሌቶች፣ የጤና ሯጮች፣ እንዲሁም አምባሳደሮች ይሳተፋበታል። በውድድሩ በሴት አትሌቶች መካከል በሚደረገው ፉክክር በአንደኝነት ለምታጠናቅቀው አትሌት የ70ሺህ ብር ሽልማት መዘጋጀቱም ታውቋል። እንዲሁም ውድድርን ሁለተኛ ሆና ለምታጠናቅቅ 45ሺህ ብር፤ 3ኛ ሆና ለምታጠናቅቅ ደግሞ የ30ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት መዘጋጀቱም ተጠቁሟል። ክብረ-ወሰን የሚያሻሽሉ አትሌቶች ተጨማሪ የገንዘብ ሽልማት የሚያገኙ ይሆናል። በውድድሩ በአትሌቶች መካከል ከሚደረገው ውድድር በተጨማሪ 15ሺህ የጤና ሯጮች እየተሳተፉ ነው። በሩጫ ውድድሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ፣ አትሌት መሰረት ደፋር እና አትሌት ለተሰንበት ግደይ ተገኝተዋል።
መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው በድጋሜ ተመርጡ
Mar 25, 2023 127
አዲስ አበባ (ኢዜአ) መጋቢት 16/2015 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ላለፉት ሶስት ዓመታት የመሩት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው በድጋሜ ተመርጡ። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዷል። በጉባኤው ቀጣይ ሶስት ዓመታት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበርን የሚመሩ የዳይሬክተሮች የቦርድ አባላት ምርጫ አካሂዷል ። በዚህም ከ15 ክለቦች እጩዎችን የቀረቡ ሲሆን ሰባቱ በአባልነት ተመርጠዋል። ሊጉን ላለፉት ሶስት ዓመታት የመሩት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ፤ ለሁለተኛ ጊዜ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተመርጠዋል። ረዳት ፕሮፌሰር ጌቱ ደጉ ምክትል ሰብሳቢ ሆነው ሲመረጡ ንዋይ በየነ፣ መንግስቱ መሀሩ፣ አብዮት ብርሃኑ፣ አሰፋ ሆሲሶ እና ልዑል ፍቃዱ የቦርድ አባል ሆነው ተመርጠዋል። በቀጣይ ሶስት ዓመት ፕሪሚየር ሊጉ የተሻለ ገቢ እንዲያመነጭና ምስራቅ አፍሪካ ላይ ጥሩ ሊግ እንዲሆን የሚሰሩ መሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ ሆነው በድጋሜ የተመርጡት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ገልጸዋል። ከሱፐር ስፖርት ጋር ውል በመግባት የቀጥታ ስርጭት ገቢ የማመንጨት ጅምሮች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰው ለሊጉ እድገት የሚያግዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ይሰራል ብለዋል። የእግር ኳስ ሜዳ ችግር ለዘርፉ እድገት ፈታኝ መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሁሉንም ትኩረት እንደሚሻ ተናግረዋል። የእግር ኳስ ሜዳዎች መገንባት የፌደራል መንግስትና የክልሎች ሃላፊነት መሆኑን ጠቅሰው በጅምር ላይ ያሉ የስታዲሞች ግንባታ እንዲጠናቀቅ መስራት ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጅራ፤ አክሲዮን ማህበሩ በተቋቋመ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም የፕሪሚየር ሊጉን የገቢ ምንጭና አቅሙን ማጠናከር ላይ በርብርብ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በምሥራቅ ባሌ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን መቀነስ ታሳቢ ያደረገ 155ሺህ ሄክታር መሬትን የሸፈነ የተፋሰስ ልማት ስራ መሰራቱ ተገለጸ
Mar 26, 2023 97
መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ) በምሥራቅ ባሌ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን መቀነስ ታሳቢ ያደረገ 155 ሺህ ሄክታር መሬትን የሸፈነ የተፋሰስ ልማት ስራ መሰራቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። በዞኑ ባለፉት ሁለት ወራት ሲካሄድ የነበረው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ መጠናቀቁን ጽህፈት ቤቱ አስታውቋል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት እንደገለጸው ባለፉት ሁለት ወራት በተከናወነው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራ 155ሺህ ሄክታር መሬት የሸፈነ የተፋሰስ ልማት ስራ ተከናውኗል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ይሳቅ በተቀናጀ የአፈርና ውኃ ጥበቃ የተከናወኑ ሥራዎች የድርቅ ተጋላጭነትን በመቀነስ በኩል ጉልህ አስታዋጽኦ እያበረከቱ ነው። በዞኑ ስምንት ወረዳዎች ከ155ሺህ ሄክታር መሬትን በመሸፈን በተከናወነው በዚህ ሥራ 3ሺህ ሄክታር መሬትን ከእንስሳት ንክኪ ማካለልን ጨምሮ የችግኝ ዝግጅት፣ 20ሺህ ኪሎ ሜትር የማሳና የተራራ ላይ እርከን ስራ፣ የግጦሽ መሬት ልማትና ሌሎች የድርቅ ተጋላጭነትን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ከድር እንዳሉት፣ በዞኑ በተደጋጋሚ እየተሰሩ የሚገኙ የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎች የድርቅ ተጋላጭነትን ከመቀነስ በተጓዳኝ የሥራ ዕድል ምንጭ እንዲሆኑ ከ4ሺህ የሚበልጡ ወጣቶችን በዘርፉ ማደራጀት ተጀምሯል። በዞኑ የዳዌ ቃቸን ወረዳ የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ አሚን እንዳሉት፣ በአካባቢያቸው በተደጋጋሚ እያጋጠመ የሚገኘውን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ ለተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ትኩረት ተሰጥቷል። በወረዳው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ የተከናወነባቸው ተፋሰሶች በዘላቂነት እንዲጠበቁ ከ30 የሚበልጡ ወጣቶችን በተፈጥሮ ኃብት ማህበራት እንዲደራጁ ተደርጓል ብለዋል። ወጣቶቹ ከእንስሳት ንክኪ በተከለሉና በተፈጥሮ ኃብት በተሸፈኑ አካባቢዎች ውስጥ የንብ ማነብ፣ የእንስሳት መኖ ልማት፣ ሌሎች የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን እንደሚያከናውኑ ነው የገለጹት። በዳዌ ቃቸን ወረዳ በአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ከተሳተፉ ነዋሪዎች መካከል አቶ ያህያ አብዱልወሃብ በሰጡት አስተያየት፣ የተቀናጀ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ሥራዎች የድርቅ ተጋላጭነትን እንደሚቀንሱ በማመን በስራው መሳተፋቸውን ተናግረዋል። በተለይ ዘንድሮ በአካባቢያቸው በተከናወኑ ሥራዎች ላይ ወጣቶች እንዲደራጁ መደረጉ ሥራውን ውጤታማ ያደርገዋል ነው ያሉት። ወጣት ሙክታር መሐመድ በበኩሉ፣ በሰው ሰራሽ ተጽእኖ የተነሳ አካባቢያቸው ተራቁቶ እንደልብ ይፈሱ የነበሩ ወንዞች በመድረቃቸው ለድርቅ መጋለጣቸውን አስታውሰዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎች የተራቆተው አካባቢ አረንጓዴ እየለበሰ መምጣቱ ተስፋ እየሰጣቸው መሆኑን ነው የገለጹት። በአሁኑ ወቅት ከሌሎች 15 የአካባቢያቸው ወጣቶች ጋር የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ማህበራት በመደራጀት በንብ ማነብና የእንስሳት መኖ እየተሳተፈ መሆኑን አመልክቷል።
በአማራ ክልል በዘንድሮው የበጋ ወራት በ331 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራ ተከናውኗል - የክልሉ ግብርና ቢሮ
Mar 24, 2023 189
ሰቆጣ መጋቢት 15 ቀን 2015(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በዘንድሮው የበጋ ወራት በ331 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራ መከናወኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ በበጋው ወቅት የተከናወኑ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎችን እንዲጠብቁ ለአርሶ አደሮች በባለቤትነት የማስረከብ መርሐግብር በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ደሃና ወረዳ ሽመላ ቀበሌ ጋውሳ ተፋሰስ ዛሬ ተካሂዷል። የአማራ ክልል የግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር አልማዝ ጊዜው የክልሉን የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ውጤታማ ለማድረግ ከ14 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የዞንና ቀበሌ ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና መሰጠቱንና 34 ሺህ የሚደርሱ የስራ መሳሪያዎች ለዞኖች መከፋፈላቸውን ለኢዜአ ገልጸዋል። በክልሉ 8 ሺህ 548 ተፋሰሶች ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራዎች ለማከናወን ታቅዶ፤ በ8 ሺህ 596 ተፋሰሶች ላይ ስራዎቹ መካሄዳቸውን አመልክተዋል። በልማቱ በ331 ሺህ ሄክታር ላይ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች መከናወናቸውንና በስራዎቹ ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። የተፈጥሮ ሃብት ልማት በዘላቂነት በማከናወን የዜጎችን ሕይወት ለመቀየር የሚያስችሉ ተግባራት ለማከናወን መታሰቡን ነው ዶክተር አልማዝ ያስረዱት። በቀጣይም የለሙ ተፋሰሶችን በስነ ሕይወታዊ ዘዴዎች የመሸፈንና የኢኮኖሚ ምንጭ የሚሆኑትን የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ እንዳሉት፤ በአስተዳደሩ በ277 ተፋሰሶች ውስጥ የሚገኝ 4 ሺህ 927 ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ተካሄዷል። በልማቱም ከ82 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውንና በዞኑ ባለፉት ዓመታት የተካሄዱት ተፋሰሶች የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እንዳሳደጉትም ገልጸዋል። በተለይም በተራራ ላይ የተሰሩ የጠረጴዛ እርከኖች ለበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንና ስራዎቹን በቀጣይም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ደሃና ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮች በአካባቢያቸው ባለፉት ዓመታት በወረዳው በተካሄዱት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች በመሳተፍ የእርሻ መሬታቸውን ለም አፈር በማሳ ውስጥ በማስቀረት ምርታማነታቸውን ማሳደግ መቻላቸውን ገልጸዋል። ዘንድሮ የተካሄዱት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራዎች በአግባቡ እንዲጠበቁና እንዲያገግሙ በየአካባቢያቸው የተፈጥሮ ሃብት ኮሚቴ ተዋቅሮ ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። በአማራ ክልል በዘንድሮው ዓመት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ሶስት ቢሊዮን ብር የሚገመት የጉልበት አስተዋጽኦ መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል'።
በአማራ ክልል የ2015 የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የሽግግርና ርክክብ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 24, 2023 149
ሰቆጣ መጋቢት 15/2015(ኢዜአ) የአማራ ክልል የ2015 የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የሽግግርና ርክክብ መርሃ ግብር በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ደሃና ወረዳ እየተካሄደ ነው። በወረዳው እየተካሄደ ባለው መርሃ ግብር የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኃይለማርያም ከፍያለውን ጨምሮ የክልልና የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በክልሉ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራው ከጥር 17 ቀን 2015 ጀምሮ ሲካሄድ ቆይቷል። ሽግግርና ርክክቡም በህዝብ ንቅናቄ የለማውን ተፋሰስ በየአቅራቢያው ለሚገኙ ነዋሪዎች በማስረከብ በስነ ህይወታዊ ዘዴ በዘላቂነት እንዲለማ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል። "ይህም ተፋሰሱን በመጠበቅና በማልማት በቋሚ አትክልትና ፍራፍሬ፣ በንብ ማነብና መሰል የሥራ ዘርፎች ተደራጅተው ለሚገቡ ወጣቶች የኢኮኖሚ ምንጭ ለመሆንም ያስችላል" ብለዋል። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በዞኑ ስድስት ወረዳዎች በ119 ቀበሌዎች በህዝብ ተሳትፎ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራዎች መካሄዳቸውን ተናግረዋል። በዚህም በ 2 ሺህ 775 ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የተሰራ ሲሆን፣ በ2 ሺህ 152 ሄክታር መሬት ላይ ደግሞ ነባር የለሙ ተፋሰሶች ጥገና መደረጉን አስታውቀዋል። በልማት ሥራው ከ82 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን የገለጹት ኃላፊው፣ በሥራዎቹ ከ147 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የጉልበት አስተዋጽኦ ማበርከት ተችሏል ብለዋል።
የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎችን ጥራትና ተደራሽነት ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል - የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
Mar 23, 2023 170
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የትንበያና የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን ጥራትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የዓለም የሚቲዎሮሎጂ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ62ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደረጃም ለ42ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተከብሯል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ክንፈ ሃይለማርያም በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎችን ለማኅበረሰቡ ተዳራሽ በማድረግ ደኅንነት ለማስጠበቅና ልማትን ለማፋጠን እየተሰራ ነው። ትክክለኛ የአየር ትንበያ መረጃዎች ለጥናት ምርምር ጭምር እንደሚያግዙ ጠቁመው ትክክለኛ የአየር ትንበያ መረጃ እንዲኖር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ጎርፍና ድርቅ ያሉ ክስተቶች በአገሪቷ እየተበራከቱ መሆናቸውን አንስተው እነዚህን ለመቋቋምም የተጠናከረ የአየር ሁኔታ መከታተያ፣ መተንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት በመገንባትና በመዘመን ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለዚህም በሰው ሃብትና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ራሱን በማሻሻል ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። በዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ ቢሮ ዳይሬክተር ዶክተር አግነስ ኪጃዚ በበኩላቸው የሚቲዎሮሎጂ ትንበያ መረጃ በተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመታገዝ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች የግብርና ሥራዎች ወቅታቸውን ጠብቀው እንዲከናወኑ ከማድረጉም ባለፈ ምርቶች በጊዜ ተሰብስበው ለተፈለገላቸው ዓላማ እንዲውሉ ከማገዝ አንጻር ሰፊ ጠቀሜታ አላቸው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 551
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
በተርኪዬ በመሬት መንቀጥቀጥ ለደረሰው ጉዳት ጥልቅ ሀዘን የተሰማው መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ
Feb 6, 2023 557
አዲስ አበባ ኢዜአ ጥር 29/2015፦በደቡባዊ ተርኪዬ በተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት፣ የአካል ጉዳት እና የንብረት መውደም የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ በሀዘን መግለጫው በአደጋው ህይወታቸውን ስላጡት ዜጎች የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፤ ጉዳት የደረሰባቸውም በቶሎ እንዲያገግሙ የመልካም ምኞት መልዕክቱን አስተላልፏል። በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያ ከቱርኪዬ መንግሥት እና ህዝብ ጎን የምትቆም መሆኗን መገለጹን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተገለጸ
Dec 20, 2022 551
አዲስ አበባ ታኅሳስ 11/2015 (ኢዜአ) አህጉራዊው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፍሪካ ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተመላከተ። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ከአፍሪካ ጋር ያላት የንግድ ትስስር ከባህረ-ሰላጤው ሃገራት መካከል በቀዳሚነት እንደሚጠቀስም ተገልጿል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዊሊያም ስቴንሀውስ ከሲ ጂ ቲ ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በተለይም ዱባይ የአፍሪካን ንግድና ኢንቨስትመንት በተመለከተ ዋና ማዕከል ሆናለች ብለዋል። በዱባይ 25ሺህ ገደማ የአፍሪካ ካምፓኒዎች እንደሚንቀሳቀሱ አመልክተው ይህም ሀገሪቱ በነጻ የንግድ ቀጣናው የቢዝነስ አጋር እንድትሆን አስችሏታል ነው ያሉት። አፍሪካውያን ባለሃብቶች የግብይት ማዕከላቸውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በማድረግና ምርቶችን ወደ አህጉሪቷ በማስገባት በነጻ ንግድ ቀጣናው ስር የገልፍ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደጉት እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የዱባይ ወደብ በአፍሪካ ያለው ተደራሽነት መስፋፋትም አፍሪካ ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የሎጀስቲክስ አቅርቦት እንደሚያሳድግ በመረጃው ተመላክቷል። ከገልፍ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት ከኢኮኖሚያዊ ትስስር ባለፈ ዲፕሎማሲያዊና ወንድማማችነትን መሠረት ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬት የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ናቸው። አምባሳደሩ እንደሚሉት ከመካከለኛው ምስራቅ መነሻቸውን ያደረጉ ባለሃብቶችና የቢዝነስ ሰዎች ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋር በልዩ ልዩ ዘርፎች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ይገኛል። እ.አ.አ በጥር 2021 ተግባራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ከአጀንዳ 2063 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቱን ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም የዲጂታል ንግድ፣ የኢንቨስትመንት ትስስርና ሌሎች የንግድ ግንኙነቶችን በነጻ የንግድ ቀጣና ለማከናውን የተካሄደ ስምምነት ነው።
የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎዛ የገዢው ፓርቲ ኤ ኤን ሲ መሪ በመሆን በድጋሚ ተመረጡ
Dec 19, 2022 516
አዲስ አበባ ታኅሳስ 10/2015 (ኢዜአ) ፦የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ገዢውአፍሪካን ናሽናል ኮንግረስ(ኤ.ኤን.ሲ) ፓርቲን በድጋሚ እንዲመሩ ተመረጡ። ፕሬዚዳንት ራማፎሳ በሁለተኛ ዙር እንደሚያሸንፉ ከምርጫው በፊት ሰፊ ግምት ተሠጥቷቸው እንደነበር የፓርቲውን ኃላፊዎች ጠቅሶ የዘገበው ኤንቢሲ ነው። በፓርቲው ስር ድምጽ ሊያገኙ ይችላሉ በሚል እውቅና ከተሰጣቸው ሌሎች እጩዎች ከፍተኛውን ድምጽ በማግኘት መመረጣቸውም በመረጃው ተመልክቷል። ፕሬዚዳንት ራማፎሳ አሁን የገዢው ፓርቲ ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸውን ተከትሎ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ፓርቲውን የሚመሩ ይሆናል።
ሐተታዎች
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 45
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
ውጣ ውረድ የማይበግረው አጋርነት
Mar 17, 2023 298
በሰለሞን ተሰራ ኢትዮጵያ በሥልጣኔ ቀደምትና ታሪካዊት ሀገር ነች። ቅሉ ከውጭ ሀገራት ያላትን ዘመናዊው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቅኝት የጀመረችው በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑ በታሪክ ይጠቀሳል። በተለይም ኢጣሊያ በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1896 በአድዋ እንዲሁም በድጋሚ በ1935 ያደረገችው የግፍ ወረራ ኢትዮጵያ የዓለምን ፖለቲካ በቅጡ አሰላለፍ ተረድታ አጋር ሀገራትን እንድትሻ ዐይኗን ገልጦላታል። በዚህም ድኅረ-አድዋ ድል በርካታ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መስርተዋል። የወቅቱ ልዕለ-ኃያል ሀገር አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷ የተመሰረተውም በዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና በፕሬዝዳንት ሩዝቬልት መንግሥት ተወካይ ሮበርት ስኪነር መካከል በፈረንጆቹ አቆጣጠር 1903 በተደረሰው የንግድ አጋርነት ስምምነት ነበር። ድኅረ-ስምምነቱም በፈረንጆቹ በ1909 የአሜሪካ ሌጋሲዮን በአዲስ አበባ የተመሰረተ ሲሆን ሆፍማን ፊሊፕ የተባሉት ቋሚ መልዕክተኛ የአሜሪካ ቆንስላ ተሿሚ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአፄ ምኒልክ አቅርበዋል፡፡ ከ120 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የኢትዮ-አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በጽኑ ወዳጅነትና የጋራ ጥቅሞች ላይ የተመሰረተ እንደነበር ይወሳል፡፡ ሀገራቱ ጥቅማቸውን በጠበቀ መልኩ የመሰረቱት ግንኙነት ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማምጣት ታሳቢ ያደረገ መሆኑም አይዘነጋም፡፡ የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራን ተከትሎ ቆንስላዋን የዘጋችው አሜሪካ፤ ኢትዮጵያ በአርበኞቿ ትግል ነፃነቷን ስታረጋግጥ በፈረንጆቹ አቆጣጠር በነኅሴ 1943 በድጋሚ ቆንስላዋን በመክፈት ግንኙነቷን አስቀጥላለች። በተመሳሳይ ወቅት ኢትዮጵያ በአሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የቆንስላ ቢሮ ከፍታ ዕውቁን ዲፕሎማት ብላታ ኤፍሬም ተወልደመድኅንን በቋሚ መልዕክተኛነት ሾማለች። በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1952 የተደረገው 'ፖይንት ፎር' የተሰኘው የተቋማት ቴክኒክ ድጋፍ ስምምነት ለሁለቱ ወዳጅ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ይበልጥ መሰረት የጣለ እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ በዚህ ስምምነትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የአውራ ጎዳና ባለሥልጣን እና የኢትዮጵያ ካርታ ሥራ ድርጅት በአሜሪካ መንግሥት ድጋፍ ተቋቁመዋል። የሁለትዮሽ ግንኙነቱ አድማሱን እያሰፋ፣ ሥር እየሰደደ ቀጥሎ ኢትዮጵያ ጦር ሠራዊቷን እንድታጠናክር በአነስተኛ የጦር መሳሪያዎች፣ ተሽከርካሪዎችና ወታደራዊ ሥልጠናዎች ተጨባጭ አጋርነት አሳይታለች። የደርግ ወታደራዊ መንግሥት ሥልጣን በተቆጣጠረ ማግስት ግን በዘመኑ በነበረው ዓለም አቀፋዊ ርዕዮተ- ዓለም ልዩነት ሳቢያ የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሻክሮ ሌላ መልክ ያዘ። በተለይም የደርግ ሊቀ-መንበር የነበሩት ሌተናል ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ወደ ሶቪየት ሕብረት አቅንተው የጦር መሳሪያ ድጋፍ መፈራረማቸው አለመግባባቱን ይበልጥ አባባሰው። በዚህም አሜሪካ በኤርትራ የነበረውን የቃኘው ሻለቃ ጣቢያዋን ዘግታ ወጣች። ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ከአምባሳደር ደረጃ በማውረድ በጉዳይ አስፈጻሚ ሲገናኙ ቆይተዋል፡፡ ኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን ሲመጣ የሀገራቱ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ቀድሞ ወደነበረበት የአምባሳደር ደረጃ በመመለስ ከአሜሪካ ጋር የነበረው ግንኙነት መልሶ እንዲያንሰራራ አድርጎታል፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት አሜሪካ በጤና፣ በሰብዓዊ ድጋፍ፣ በመልካም አስተዳደርና በዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ላይ በምታደረገው ድጋፍ በመታገዝ በጋራ ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ ከሦስት ዓመታት ወዲህ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ አሜሪካ መርህን ያልተከተለ አካሄድ በሀገራቱ መካከል የነበረውን ወዳጅነትና አጋርነት ላይ ጥቁር ጥላ ማጥላቱ አይዘነጋም፡፡ ነገር ግን ባለፉት ሦስት ዓመታት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ሻክሮ የቆየውን ግንኙነት በማደስ የነበረውን ጠንካራ ወዳጅነት በድጋሚ የሚያጸኑ ጅማሮዎች ተስተውለዋል። በተለይም ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የተደረሰውን የሰላም ሰምምነት ተከትሎ የሀገራቱ መቃቃር እየረገበ ሲሆን የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ኢትዮጵያን በተደጋጋሚ እየጎበኙ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ከትናንት በስቲያ አዲስ አበባ የገቡት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፤ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ተነጋግረዋል። አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ያደረጉት ውይይት ዘርፈ-ብዙ አጋርነትን ለማጠናከር መግባባት የተደረሰበት እንደነበርም በሁለቱም ወገኖች ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ውይይቱ በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደሆነና በኢትዮጵያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ስምምነት የተደረሰበት እንደሆነ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት ማግኘቱንም ጠቅሰዋል። በኢኮኖሚው መስክ በተለይም በግብርና እና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ባተኮሩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት መነጋገራቸውን በመልዕክታቸው ጠቁመዋል። በተመሳሳይ አንቶኒ ብሊንከን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ባደረጉት በሁለትዮሽና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በትኩረት መክረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ሚኒስትሮቹ ለረዥም ዘመን የዘለቀውን የኢትዮ-አሜሪካ ትብብር እና አጋርነት ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ተነጋግረዋል። በኢትዮጵያ አዲስ የመረጋጋትና የሰላም ምዕራፍ መከፈቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን አብራርተውላቸዋል። የሰላም ምዕራፍ የበለጠ እንዲጠናከርና የሰመረ እንዲሆን ከዚህ ባለፈም የሀገሪቱን በጎ ገጽታ እንዲላበስ መንግሥት በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ እምርታ እንዲመጣ ለሰላም ስምምነቱ ተፈፃሚነት መንግሥት አሁንም ቁርጠኛና ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ጠቅሰው፤ በመልሶ ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም ተግባር የአሜሪካ መንግሥት እንዲደግፍም ጠይቀዋል፡፡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በበኩላቸው፤ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሻገር አሜሪካ በትብብር መንፈስ እንደምትሰራ እና አሜሪካ ሁለንተናዊ ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። አሜሪካ ለድርቅ ተጎጂዎች እና ለስደተኞች የምታደርገው ድጋፍ አለመቋረጡ የሁለቱ ሀገራት አብሮነት ተጠናክሮ መቀጠሉን ይጠቁማል፡፡ የብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝት ከኢትዮጵያ መጀመሩም ዛሬም ኢትዮጵያ በአሜሪካ መንግሥት ዐይን ያላትን ቀዳሚ ሥፍራ ያመለክታል። አንቶኒ ብሊንከን የሰላም ትግበራ ሂደቱ በመልካም ሁኔታ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ የበለጠ እንዲጠናከር የአሜሪካ መንግሥት ሁለገብ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የሁለቱን ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆኑን ማረጋገጡን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ እያደረገች ያለውን ጥረት አሜሪካ በአድናቆት እንደምትመለከተውና የሚበረታታ መሆኑን ብሊንከን ገልጸዋል። የብሊንከንን ጉብኝት ተከትሎ አሜሪካ 331 ሚሊየን ዶላር ተጨማሪ የሰብዓዊ ድጋፍ ለኢትዮጵያ እንደምታደርግ አረጋግጣለች። ድጋፉም በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ወገኖች ነፍስ አድን ሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።
የሴቶች ቀን ሲታሰብ
Mar 8, 2023 489
የሴቶች ቀን ሲታሰብ የሰው ልጅ ሕይወትን ቀላል ባደረጉ የፈጠራ ስራዎቻቸው የምናስባቸው እንስቶች በቀዳሚነት ይነሳሉ። በተለያዩ መስኮች አሻራቸውን ያሳረፉ እንስቶች ቁጥራቸው ከፍተኛ ቢሆንም በዚህ ጽሑፋችን ግን በኬሚስትሪና ፊዚክስ ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ ባበረከቱት አስተዋጽኦ በኖቤል ሽልማት እውቅና የተሰጣቸውን የየዘመኑ ፈርጦች እንዳስሳለን። ከነዚህ ፈርጦች መካከል በኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤልን ሽልማትን ከሴቶች ቀዳሚ በመሆን በቀዳሚነት ያሸነፉት ሜሪ ኩሪ ይወሳሉ። ይልቁንም እ.አ.አ በ1903 በኬሚስትሪ ዘርፍ የተቀበሉትን የኖቤል ሽልማት በድጋሚ በ1911 በመሸለም ብቸኛነት ስማቸው ይነሳል። በ1967 በፖላንድ ዋርሶ የተወለዱት ማሪ ኩሪ ለዘመናዊው የሳይንስና ኬሚስትሪ ዘርፍ ውለታን ከዋሉ ስመጥር ተመራማሪዎችና በጨረራ ህክምና ፈጠራ የዘርፉ ፈር ቀዳጅ በመሆን የአለምን የራዲዮአክቲቪቲ እይታን የቀየሩ ጀግና ናቸው። የሜካኒካልና ኤሮስፔስ ተመራማሪዋ ፍራንሲስ አርኖልድ ደግሞ በህክምናናና በታዳሽ ኃይል ዘርፍ አሻረቸውን በጉልህ ካኖሩ ተመራማሪዎች መካከል ይጠቀሳሉ። አሜሪካዊቷ ፍራንሲስ ለታዳሽ ኃይል እና ለፋርማሲ አገልግሎት የሚውል አዲስ ኢንዛይም በምርምር በማግኘት በዘረፉ አሻራቸውን አኑረዋል። ለዚህም አስተዋጽኦዋ እ.አ.አ በ2018 በኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤልን ሽልማት አሸንፈዋል። የኤድስን ስርጭትን በመከላከል ረገድ ሰፊ አበርክቶ ያላቸው የህክምና ተመራማሪዋ ፍራንሶዝ ባሪሲኖሲም የሴቶች ቀን ሲታሰብ ከሚወሱ አንስቶች አንደኛዋ ናቸው። ባሪሲኖሲ የኤች አይቪ ኤድስን ከገዳይ በሽታነት መታከምና መቆጣጠር ወደ ሚችል በሽታነት ለመቀየር የኤች አይቪ ኤድስ ምርመራን በማላቅ ረገድ ሚናቸው የጎላ እንደሆነ ይወሳል። በ1947 በፓሪስ ከተማ የተወለዱት ባሪሲኖሲ “ሳይንስን ለሰው ልጆች ጥቅም እንዲውል እንሰራለን” በሚለው አባባላቸው ይታወቃሉ። ኤድስን በመከላከል ላደረጉት አስተዋጽኦም በፊዚዮሎጂ/ሕክምና ዘርፍ እ.አ.አ በ2008 የኖቤል ሽልማትን አግኝተዋል። ያለ ህክምና ትምህርት የሚሊዮኖችን ሕይወት በታደገው የወባ በሽታ መከላከያ ፈጠራቸው አለም እውቅና የተሰጣቸው ቱ ዩዩ በሴቶች ቀን የምናመሰግናቸው ሌላኛዋ ተመራማሪ ናቸው። ቻይናዊቷ ቱ ዩዩ ባህላዊውን የወባ በሽታ መከለከያ ህክምና ወደ ዘመናዊ በመቀየርና በማስተዋወቅ ነው ስመ ገናና የሆኑት። የወባ በሽታን በመከላከል ረገድ በአለም አቀፍ ደረጃ ጉዙፍ አሻራቸውን ላስቀመጡት ተመራማሪ ባለውለታነት እ.አ.አ በ2015 በፊዚዎሎጂ/ ህክምና ዘርፍ ሳይንስ ምድብ የመጀመሪያዋ ቻይናዊት በመሆን የኖቤል ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የሰው ልጆችን ሕይወት ካቀለሉ አለም አቀፍ ፈጠራዎች መካከል የተጠቀሱትን ጨምሮ በሌሎችም ዘርፎች የሴቶች ተሳትፎ የጎላ መሆኑ ይታወቃል።
ሴትነት እና እናትነት
Mar 8, 2023 721
(አየለ ያረጋል) እስኪ መላ ስጪኝ መላ ካንቺ ይገኛል እኔማ ወንድ ነኝ ይደናገረኛል… (የማኅበረሰቡ ቃላዊ ግጥም) ሴትነት እናትነትን ለመግለጽ ቀርቶ በጥቂቱ ለመረዳት የ’እናት ልብ’ መታደል የሚሻ ይመስላል። ጥቂት ወንዶች ይህን ጸጋ ይቸራሉ። ልክ እንደ ዶክተር ይሁኔ አየለ። የስነ-ምግብ ሳይንቲስቱ ዶክተር ይሁኔ አየለ ‘እናት’ በሚል ርዕስ ባሳተሙት ድንቅ መጽሐፍ የሴትነት እና እናትነትን ከፍታ በ’ኩርሽም’ ቃላት ተራቀውበታል። የሴቶች ቀንን (ማርች-8) ሰበብ በማድረግ ይህን ጽሑፍ ሳዘጋጅ መታሰቢያነቱ እናትን አስበው በ‘እናትነት’ ቅን ልቦና ‘እናትን’ ላበረከቱልን ዶክተር ይሁኔ አየለ ነው። ‘እናት፤ የሴት ልጅ ስንክሳር፤ ከቤተሰባዊ ሕይወት እስከ ሐልዮመንበርት’ በሚል ርዕስ በቅርቡ ባሳተሙት (በ406 ገፆች በተቀነበበ) አርበ ጠባብ መጽሐፍ ሴትነትን ከዘፍጥረት እስከ አሁን ዘመናትን ዋጅተው፣ እናትነትን ከሴትነት ዘንቀው፣ የእናትነት ጸጋን ከነባራዊ ሃቅ ጋር አሰነናስለው፣ የእናትነትን ልዕለ-ተፈጥሮ አርቅቀው፣ የዓለምን ክብር-ነሽነት ከነገረ-ሃይማኖት እስከ ነገረ-ባህልና ፍልስፍና ፈትተው፣ የማኅበረሰቡን ምልከታ ዝንፈት እና ሚዛን ጉድለት ከማኅበራዊ እስከ ፖለቲካዊ መገለጫዎች አዛምደው አቅርበውታል። ዶክተር ይሁኔ አየለ “እናት” በተሰኘ እናት የሆነ መጽሐፋቸው እናትነትን በልኩ ነጽረውታል። ሴትነት በኢትዮጵያ የአስተሳሰብ ሰለባነቱን፣ ነገረ-ሴትነትን ከንጽረተ-ሴትነት ቃኝተውታል። በእሳቤ ሚዛን ሰለባነት ዓለም ውስጥ ከንግስት ማክዳ እስከ ንግስት ፉራ፣ ከሰብለ ወንጌል እስከ ድል ወንበራ፣ … ብርቱ ኢትዮጵያዊት ሴቶችን ሕይወት ጨልፈውታል። የሴትነትን ጸጋዎች ጨልፈው በሴትነት ላይ የሚፈጸሙ የሀበሻ ግፎችን ተንትነውበታል። ሴቶች የማኅበረሰቡ ግፍ ሰለባዎች፣ የማኅበራዊ ፍትህ ጉድለት ሰለባዎች እንደሆኑ በቅጡ ገልጸውታል። ዳሩ ሴትነት ጀግና እና ብልህ፣ የቤተሰብ መሰረት፣ የደስታና እልልታ እናት፣ ቃል ኪዳንና ክብር ጠባቂ እንደሆነ ገልጸዋል። “ሴት ልጅ ባለብዙ ጸጋዎች ናት። ከጸጋዎቿ መካከል ጀግንነት እና ብልሃት ይጠቀሳሉ። … ሴት ልጅ ባህልን ፈጥራ የማኅበራዊነትን ማስተሳሰሪያ ገመዶች ገምዳ አስተሳስራ ማኅበረሰብን የተከለች ሥርዓት ናት። … ቤተሰብ የአንድ ማኅበረሰብ የመጀመሪያ ተቋም ነው። የተቋሙ ባለሥልጣን (እመቤት) ሴት ናት። ያቺ ሴት እናት ናት። ቤተሰብ የስብዕና መሰረት የሚባለው እናትን ምሰሶ አድርጎ ነው” (ገጽ-285) ሴት ልጅ መለኛ መሆኗን ማኅበረሰባችን ቢያምንም ሴትነትን ግን እንዳላከበረ አሉታዊ ይትባህልና ኪነተ- ቃሉን ዘይቤ ያወሳሉ። በእርግጥ የእናትን ምቹነት እና ዋጋ ከፋይነት የሚያትቱ የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎችም አሉ። ለምሳሌ ዳንኤል አበራ “የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎች” በሚለው መጽሐፋቸው “እናት ትረገጣለች እንደመሬት፤ እናት ለልጄ ልጅ ለነገዬ፤ እናቷን አይተህ ልጅቷን አግባ፤ እናት የሌለው ልጅ እንደ ጌሾ፤ ሳይበላ የበላ ሳይናገር ዋሾ…” የሚሉ ምሳሌያዊ ንግግሮችን አስፍረዋል። መላኩ ይርዳው የተባሉ ጸሐፊ ‘ደቦ ቅጽ-፩’ ከተሰኘው የ60 ደራሲያን ሥራዎችን ያካተተ መጽሐፍ ውስጥ ‘የሴትነት ጸጋ’ በሚል በጻፉት መጣጥፍ ሴትነትን ከፍቅር፣ ከጥበብ፣ ከብልሃትና ልዕልና ጋር አቆራኝተውታል። “ሴት ልጅ ቅኔ ናት፤ ከተባለላት፣ ከተጻፈላት፣ ከተዜመላት በላይ የረቀቀች ረቂቅ ቅኔ ናት። እስከዛሬ ከያኒያን ስለሴት ከተራቀቁት፣ ከተጠበቡት ሁሉ እኔ ለማውቃት ሴት ሁሉ የሚመጥኑ ሆነው አልታዩኝም። የሴትነት ጸጋው ብዙ ነውና የሴትን ትክክለኛ ማንነት መርምረን አጥንተን የደረስንበት ውስጠ-ስሪቷን አጥንተን የተረዳነው አይመስለኝም።… ከታላቅነቷ፣ ከብልሃቷ፣ ከረቂቅነቷ፣ ከመግዛት አቅሟ፣ ከርህራሄዋ፣ ከሰላማዊነቷ ከሌሎችም አያሌ በረከቶች አንጻር ለሴት ልጅ የተደረገላት፣ የተነገረላትና የሆነላት ሁሉ ያንስብኛል” ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) ስለሴት ልጅ ጭቆና የታገለ እና ስለክብሯ የዘመረ ምሁር ነው። ስለሴት ልጅ ስቃይና ሰቆቃ አትቷል። ‘በናቴኮ ሴት ነኝ’ በሚለው መጽሐፉ ስንኞች እንምዘዝ! …. ግማሽ አካሏ ወንድ በትምክህት ቢከዳት ጧ! ብላ አለቀሰች አዛኝ ቢደርስላት፣ … ብሶት ተጫጭኗት ምንም ሰው አልሆነች በቀቢጸ ተስፋ ሕላዌንም ጠላች ያገሬ ጭቁን ሴት መድኅን መላ ያጣች….! ‘ሔዋንያት የትውልድ ፋብሪካዎች ናቸው፤ እነሱ ባይኖሩ ዓለም ባዶ ትሆን ነበር’ እንዲል ፈላስፋው ሶቅራጥስ። ስለሴት (ግማደ ሰቧ ፍጡር) ግፍና በደል ገሞራው እንዲህ ይላል። “መራራ ጭቆና በሰፈነበት ምዝብር ሕብረተሰብ ውስጥ ታፍነው የሚኖሩ ሔዋንያት ብሶታቸው፣ ፍዳቸው፣ በደላቸው፣ ጭንቀታቸውና መከራቸው እንደ ሰማዕታት ገድል እጥፍ ድርብ ነው…. አጉል ልማድ፣ ኋላቀር ባሕልና አድሃሪ ሕገ-ማኅበረሰብ ከከንቱ አስተሳሰቦች ጋር ተዳምሮ በአንድነት በመመሳጠር ዘርዓ ሔዋንን ሲጫወቱባቸው ሲያሾፉባቸው ኑረዋል” (ገጽ-23) በሥነ-ሕይወት ሳይንስና በትምህርተ-ጄነቲክስ (አካለ ሕላዌ) ሴቶችን ከወንዶች የሚያሳንስ ምንም አይነት አካላዊ ተሰጥኦ እንደሌለ ተረጋግጧል። ታሪክና ተረክ ግን ወገንተኛ መሆኑን ገሞራው ይናገራል። ተረክና ተረት አልባሌ ታሪክ የሚፈጥሯቸው አርበኞች ሁሉ በፆታቸው ተባዕት በመሆናቸው፤ በሴቶች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ በማሳደሩ ሊኖራቸው የሚችለው ዕድገት ላይ ትልቅ ደንቃራ ሆኖ መቆየቱን ይገልጻል። “የታሪክን ሁኔታዎችን የመመንዘር ትርጓሜያዊ አንጻር የታሪክን ትዕይንቶች ብንመረምር አንደርድሮ የሚያደርሰን ሴቶች ከወንዶች የከፋ ባህሪያዊ ድክመት እንዳለባቸው ከሚያሳይ ሥዕል ላይ ነው።” በሚት(ተለጣጭ ተረክ) ላይ የሚራቀቁት አቶ ቴዎድሮስ ገብሬ (በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፎክለር መምህር) ‘ተረኮች እማዊ ሳይሆን አባዊ ናቸው’ በማለት ይህን ጉዳይ ያጠናክሩታል። “በሚት ውስጥ ገነው ከሚታዩ አበይት ማኅበራዊና ባህላዊ እውነታዎች መሃል አንዱ ፆታዊ ወገንተኝነት ነው። የሰማናቸው፣ ያነበብናቸው ሚታዊ ተረኮች በእጅጉ አባዊ ለሆኑ ሥርዓቶች (ፓትሪያርካል ሲስተምስ) ያደሩ፣ በአብዛኛው በተባዕት ተጋዳሊያን የተሞሉ ናቸው” ይላል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዶክተር ይሁኔ (በገፅ-401) ስለሰው ማንነት ቀረጻ በተመለከተ ከጥንት እስከ ዛሬ አከራካሪ የሆኑ ፈላስፎችን ክርክር ያነሳሉ። ይኸውም የሰው ልጅ ‘ማን ቀረጸኝ? ተፈጥሮ ወይስ ተሞክሮ?’ የሚለውን መከራከሪያ ጽንሰ-ሃሳብ ይፈትሻሉ። በዚህም “ሰዎች ሲፈጠሩ የሰውየውን ችሎታ ይዘው ነው” እና “የሰዎች ማንነት የሚቀረጸው ከውልደት በኋላ በተሞክሮ ወይም ከአካባቢ ጋር በሚኖራቸው መስተጋብር ነው” የሚሉትን ሃሳቦች ወስደው ከእናት ሚና ጋር ያዛምዱታል። እናም እናት ‘በየትኛውም መደብ ልጅን አሳምራ ትቀርጻለች’ የሚል ድምዳሜ ሰጥተዋል። “በየትኛውም መንገድ በሰው ልጅ ላይ የእናት ቀራፂነት ስለሚኖር ከተጽዕኖዋ ማምለጥ የሚቻል አይመስለኝም።… አካባቢም ሰውን ይሰራዋል የሚሉትም ከውልደት በፊትም ሆነ በኋላ ከተፈጥሮ ጋር የሚደረገው ውስብስብ መስተጋብር ‘ሰው’ በመሆን ላይ ጉልህ ሚና ይጫወታል” ይላሉ። በዚህ እሳቤ ሰው የወላጆቹም፤ የአካባቢውም ውጤት መሆኑን በግልጽ እንረዳለን” ይላሉ። ሴቶች ከጥንት እስከ ዛሬ በኢትዮጵያ ማኅበረ-ባህላዊ እንዲሁም ለሰላምና ዕርቅ እሴቶች ጉልህ ሚና አላቸው። ሴቶች ያልተሳተፉበት ዘርፍ የለም። ከመሪነት፣ ጥበበኝነት፣ ከአገር ድንበር ጠባቂነትና የዲፕሎማሲያዊ ሚና… መጥቀስ ይቻላል። ሴቶች በሁሉም ማኅበረሰብ ዘንድ በሰላምና ግጭት አፈታት ግንባር ቀደም ተሰሚነት አላቸው። ለአብነትም ሀደ ሲንቄ፣ በሶማሌ-ሔር፣ በሲዳማ-ያካ፣ በራያ ማኅበረሰብ ዱበርቲዎች፣ በስልጤ-ሴረን ባህል መጥቀስ ይቻላል። ከሰሞኑ ባከበርነው የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ሴቶች ውለታ በወፍ በረር ማውሳት ይቻላል። የኢትዮጵያ ሴቶች ከሌላው ዓለም ሴቶች በተለየ የራሳቸው ቀለም ያላቸው፣ የአመራር ልምድ ያዳበሩ፣ የመወዳደሪያ ስነ-ልቦና ያላቸው፣ ችለው አሸንፈው ያሳዩ ናቸው። ሴቶች ድሉን በማስመዝገብ የተጫወቱትን ሚና ያህል፣ ገድላቸው በታሪክ በሚገባ አልተወሳም። ዶክተር አልማው ክፍሌ የተባሉ የታሪክ ምሁር በአንድ ወቅት ሚዲያ ላይ ቀርበው “በአድዋ ጦርነት ዘማቾች 75 በመቶ ሴቶች ነበሩ” ሲሉ ሰምቻለሁ። በአድዋ ጦርነት ሴቶች በተለያዩ ሙያዎች ተመድበው ከካምፕ እስከ ጦር ሜዳ ከመመገብ እስከ ማጀገን፣ ከማከም እስከ መዋጋት ድንቅ ሚና ተወጥተዋል። ድርብ ድርብርብ ኃላፊነት ይዘው የዘመቱ፣ ለወንዶችም ልብ፣ ሞራልና ወኔ አቀባዮች ነበሩ። እቴጌ ጣይቱን መሰል የአድዋ ሴት የጦር ፊታውራሪዎች በርካታ ናቸው። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ ወልደአረጋይ ‘ታሪክ ዘመን ዘዳግማዊ ምኒልክ’ በተሰኘው መጽሐፋቸው የሴቶችን ሚና በተመለከተ እንዲህ ይላሉ፡- “እንዲህም እየሆነ፣ አጤ ምኒልክ ባዳራሹ እቴጌ ጣይቱ በእልፍኝ ባለሟሎችዎን ወይዛዝርቱን ይዘው ግብሩ አንድ ቀን ሳይጎድል፣ ይዘምታሉ። ከዘመቻ ላይ ጠጁ ማሩ አለመጉደሉ፣ ስለምንድነው ያልህ እንደሆነ ይህን ታሪክ መመልከት ነው። በስድስት ድንኳን እንጀራው ሲጋገር ሲያድር፣ በአራት ድንኳን ወጡ ሲሠራ ሲያድር፣ ጠጁ በቀንድ በኮዳ ደግሞ ሦስት መቶ ስድስት መቶ የሚሆን ገንቦኛ ሲጓዝ ግብሩ ይጎድል ይመስልሀል” (ገጽ-241) ደራሲ በዕውቀቱ ሥዩም ‘ከአሜን ባሻገር’ በተሰኘ መጽሐፉ ‘ሴቶች በዋሉበት’ በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ሴቶች ተጋድሎና ሚና “ከቁስ ባሻገር ከልብ ያቀርባሉ” ይላቸዋል። “ሴቶች ባዋላጅነት ከነበራቸው የማይተናነስ ሚና በጦር ሜዳ ተጫውተዋል። እናቶቻችን በጦር ወቅት፣ መሳሪያ ያቀርቡ ነበር። ምግብ ያቀርቡ ነበር። ሃሳብ ያቀርቡ ነበር። ልብ ያቀርቡ ነበር። ደስታ ያቀርቡ ነበር። ኧረ ምኑ ቅጡ። ሴቶች ባንድ በሙቀጫ ዙሪያ፣ ማኅበረሰቡን ኬሚስት፣ ገጣሚና የፖለቲካ ተንታኝ ሆነው ማገልገላቸውን ልብ እንበል” ይላል። (ገጽ-138) ዶክተር ይሁኔ (በገጽ-14) በበኩላቸው እናቶችን ሩህሩሆች፣ አጉራሽና አልባሽ፣ የችግር ቤዛዎች፣ ሕይወት ዑደት አስቀጣዮች፣ የሕይወት መድኅኖች፣ ባለብዙ ጸጋዎች፣ መልካም ባህሪ አውራሾች፣… በማለት ገልጸውታል። መላ ሴቶችንም በእናቶች አተያይ ማየት እንደሚገባም እንዲሁ። “እናትነት መልካም ገጽታዎችን ደራርቦ የያዘ የሴት ልጅ ትልቅ መገለጫ ነው። እናትነት ከፍ ያለ ሥልጣን ነው። እናትነት ጥልቅና ሰናይ ባህሪያት የሚፈልቁበት ምንጭ ነው። እናትነት የደግነት፣ የጥራት፣ የልህቀትና ተፈላጊነት ማሳያ ተምሳሌት ነው። እናትነት ሞት የማያደበዝዘው ኃያል መንፈስ ነው። እናትነት ከባድ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነው። … እናትነት የሰላም፣ የመልካም ግንኙነትና እንክብካቤ መፍለቂያ አድባር ናት። እናትነት ሰፊና ጥልቅ የሕይወት ትምህርት ቤት ነው። እናትነት ሌሎች ከስቃይ ነፃ እንዲሆኑ፣ ምቾት እንዲሰማቸው በሚደረግ ትግል ውስጥ ዋጋ እየከፈሉ መኖር ነው” በመቀጠልም የኢትዮጵያ እናቶችን ‘ጠቃሚ ነገር ሰጪዎች’ ይላቸዋል። “እናቶች ሰው የመሆኛ ቅመሞች የሚጨለፍባቸው ባህር ናቸው። … ሕይወታዊ ስሪታችን ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን የወሰደው ከእናት ነው። ከእናት የምናገኘው ‘ማይቶኮንድሪያ’ (ማይቶኮንድሪያ የኃይል ማመንጫ ክፍል ሲሆን የምንመገበው ምግብ እየተቃጠለና ወደ አስፈላጊው ኃይል እየተቀየረ ሕይወትን ያንቀሳቅሳል) የምግብ ማቃጠያ ምድጃ ወይም ኃይል ማመንጫ ቤት ሆኖ ያገለግላል። … ብዙ መልካም ስብዕና መገለጫዎች ምንጫቸው የእናት ፍቅር፣ የመልካም ስብዕና እና የርህራሄ ምንጭ ነው” (ገጽ- 61) ኢያሱ በካፋ ‘የኢያሱ በካፋ ወጎች’ በተሰኘው መጽሐፉ እናትነትን ማህጸንን፣ ምግብን፣ ትንፋሽን፣ ደም፣ ሥጋን እና ነፍስን ሰጥተው በረቂቅ ተፈጥሮ ሰውን ከመውለድ ባለፈ ፍቅራቸውን ዘላለማዊ ገደብ አልባ እና ዕልቆ-ቢስ እንደሆነ እንዲህ ገልጾታል። “እናትነት ነፍስን ማካፈል ነው፤ እናትነት የማይደበዝዝ ዘላለማዊ ፍቅር መስጠት ነው፤ እናትነት ከራስ ሕልውና ይበልጥ ለልጅ ማሰብ ነው፤ እናትነት ፍፁም ወረት አልባ መሆን ነው። እናት ለልጇ ያላት ፍቅር አይነጥፍም፤ አይለወጥም። ለእናት ልጇ ሁሌም ልጇ ነው” (ገጽ-4) እናትነት በቃላት ለመግለጽ እንደሚከብድ፤ በውለታ ማካካስ ይከብዳል። የእናት ውለታዋን መክፈል የሚችል ልጅ የለም። የእናት ፍቅርን ለመግለጽም በርካቶች አንደበታቸው ይተሳሰራል፤ ቃላት ይነጥፍባቸዋል፤ ስሜታቸውን መግራት ይሳናቸዋል። ድምፃዊ እሱባለው ይታየው(የሺ) ‘ይናገራል ፎቶ’ በሚል እናትና አባቱን በገለጸበት ሙዚቃ የመጨረሻው ማጠንጠኛው ‘እወድሻለሁ/እወድሃለሁ’ ያለው፤ እንዲሁም ድምፃዊት ብዙነሽ በቀለ ‘እናት ውለታዋ’ በተሰኘ ዘፈኗ ውስጥ (ዜማና ግጥም ጋዜጠኛ ሰለሞን ተሰማ)፤ “ወላጅ እናት እኮ ፍፁም በመንፈሷ፣ ልጇን ትወዳለች አብልጣ ከራሷ” እያለች በሚስረቀረቅ ድምጿ የምታንጎራጉረው ለዚህ ይመስላል። ዕውቁ የቋንቋ ሊቅ የሻው ተሰማ (የኮተቤው) ‘የጥቁር አፈር ትሩፋቶች’ በተሰኘው መጽሐፉ (ገጽ-79) ‘መቀነትሽን አጥብቂ’ በሚል ርዕስ ባሰፈረው ረዘም ያለ ግጥም ሁለት አንጓዎች ብቻ ስንመዝ የእናትነት ውለታን መመለስ እንደሚሳን፤ የእናትነት ግብሯ ‘እናት’ የሚለው ቃል በራሱ እንደሚያንስባት ያትታል። … “ለዚህ ወሮታሽ አጸፋ፤ እናት ይልሻል አገሩ፤ እኔም እናቴ ብልሽ መች ሊመጥንሽ ዳሩ። … እናትነት ምጡቅ ነው፤ እናት ከመባል ይልቃል፤ የግብርሽ ስንክሳር ዚቁ፤ በስያሜ መች ያልቃል”… በማለት ይገልጸዋል። መውጫ ዶክተር ይሁኔ የሴት እና እናትን የነገዋን መንገድ ከሳይንስ አተያይ አንጽረው፤ ከማኅበረ-ፖለቲካ፤ ከማኅበረ-ባህል ከፍታዋ አመሳክረው፤ እናትና ሀገርን መጋመድ አመስጥረው መልእክታቸውን እንደ መውጫ አስፍረዋል። ለስንበት አንድ አንቀጽ እንወርውር!! “የእናት ሀገር ህልውና ከእናቶች ሕይወት ጋር በቀጥተኛ ተዛምዶ አለው። የሰመረ ትውልድ ሊቀጠል የሚችለው በጥሩ ሁኔታ በተገነባ የእናቶች አቅም ነው። የእናቶች አቅም ሲገነባ የራሳቸውን አቅም ያውቃሉ፤ ምርጫቸውን በራሳቸው ይወስናሉ፤ እንዲሁም ለሚመጣው ማኅበራዊ ለውጥ የራሳቸውን አሻራ ያሳርፋሉ። ስለሆነም የእናቶችን አቅም ማጎልበት ትውልድን ማጎልበት ነው። እናቶች ላይ መሥራት ትውልድ ላይ መሥራት ነው”
ትንታኔዎች
የአየር ንብረት ፋይናንስ-አፍሪካውያን ገፍተው ያልሄዱበት መንገድ
Feb 18, 2023 570
/በገዛኸኝ ደገፉ/ የአፍሪካ ቀንድ ከ40 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ አያቅም የተባለለትን የድርቅ አደጋ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ሆነዋል። የድርቁ አደጋ የከፋበት የአፍሪካ ቀንድ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ተሸክመዋል። በተጨማሪም የከተሞች መስፋፋትና የከተሜነት የኑሮ ዘይቤን እያስተናገደች ባለችው አፍሪካ የኃይል እጥረት፣ በቂ የመሰረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ አለመኖር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት፣ ሥራ አጥነት ብሎም የወንጀሎች መስፋፋት አሕጉሪቱን ክፉኛ እየፈተኗት ይገኛሉ። የገጠር መሬት ምርታማነት መቀነስ ከገጠር ወደ ከተማ ለሚደረገው ፍልሰት አንደኛው ገፊ ምክንያት ሲሆን ለመሬቱ ምርታማነት መቀነስ ሰበብ ተደርጎ በዋናነት የሚጠቀሰው ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት የሚወልዳቸው የውኃ ኃብት መቀነስና ለተከታታይ ዓመታት የሚዘልቁት የድርቅ አደጋዎች መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አወሳስቦታል። እንደ አህጉር ከ4 በመቶ ያነሰ የካርቦን ልቀት ያላት አፍሪካ 65 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ መሆን ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚህ ችግር ሙሉ ለሙሉ መውጣት ባይቻልም ትርጉም ባለው ደረጃ መቀነስ እንዲቻል አህጉሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ኃብትና ወጣት የሰው ኃይል በማስተሳሰር ለውጥ ማምጣት ግድ ይላታል። በአፍሪካ የማይቀረውን የከተሞች መስፋፋትም ሆነ የህዝቦቿን የመልማትና የመለውጥ ፍላጎት ማሟላት ካለባት የአየር ንብረት ፋይናንስን የበለፀጉ ሀገራት ገቢራዊ ሊያደርጉት ይገባል። የአየር ንብረት ፋይናንስ (Climate Finance) የአካባቢ፣ ብሔራዊ ወይም ድንበር ተሻጋሪ ፋይናንስን የሚመለከት ሲሆን ከሕዝብ፣ ከግል እና ከአማራጭ የገንዘብ ምንጮች የተውጣጣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ስምምነት ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል እና የፓሪስ ስምምነት ደግሞ ሰፊ የገንዘብ አቅም ካላቸው አገራት አነስተኛ የኃብት አቅም ላላቸው እና ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ አገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት ነው። ስምምነቱ “የጋራ ግን ደግሞ ልዩነት ያለው ኃላፊነትና አቅም” በሚለው መርህ መሰረት ያደጉ አገሮች አዳጊ አገራትን ለመርዳት የገንዘብ ምንጮችን እንዲያቀርቡ ይጠይቃል። ፋይናንሱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ወሳኝ ድጋፍ እንደሚሆን ታምኖበታል። ምክንያቱም ልቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ላቅ ያለ የኢንቨስትመንት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ። በተመሳሳይ ከአሉታዊ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎች ጋር ለመላመድ እና ተለዋዋጭ ጫናዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። ከጥቂት አሥርት ዓመታት በፊት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የምእተ ዓመቱ የልማት ግብ ሰነድም ሆነ በቅርቡ በሚጠናቀቀው ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት ቢሰጠውም እስካሁን ግን የፈየደው ነገር የለም። አፍሪካ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችን ለመላመድ ዓመታዊ 41 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ክፍተት ይገጥማታል። ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ እያስተናገደች ባለችው 36ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ የአየር ንብረት ፋይናንስ ገቢራዊ ማድረግን ቀዳሚ ትኩረታቸው መሆን እንዳለበት የአንድ ዘመቻ (ONE Campaign) አጽንኦት ሰጥቶ ምክረ ሃሳቡን ሰንዝሯል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የአንድ ዘመቻ ዳይሬክተር ዶሪን ኒኒናሃዝዌ የአፍሪካ መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመላመድ ፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን አስከፊ ተጽዕኖ የመቋቋም አቅም እንዲገነቡ መክረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝቦቿ ለከፋ ጥቃት እየተዳረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች የበለጸጉ አገሮች የገቡትን የማላመድ ፋይናንስ ድጋፍ ቃል እንዲፈጽሙ ከማግባባት ባለፈ ማሳሰብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ ማለት እኤአ ከ2020 እስከ 2025 በዓመት 100 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመተውን ግብ የማሳካት ተግባር የሚጠይቅ ነው። ከዚህ ባሻገር በቀጣዮቹ ዓመታት በተጨመሩ መዋጮዎች የሚስተዋሉ ጉድለቶችን መፍታት እና በግብጿ ሻርም ኤል ሼክ ከተማ ባስተናገደችው COP-27 ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ለመላመድ በእጥፍ ፋይናንስን የማቅረብ ቁርጠኝነት የማቅረቢያ ዕቅድ ሊነድፉ ይገባል ነው ያሉት። የአፍሪካ አገሮች ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ጋር ሲታገሉ ቢቆዩም አሁን ላይ “አፍሪካ በአፈፃጸሙ ላይ መጠነኛ መሻሻል አሳይታለች” ብለዋል። እናም በ36ኛው የመሪዎቹ ጉባዔ የተገኙ ስኬቶች እና የጠፉ ዕድሎች እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማዎች ለማሳካት በአየር ንብረት ፋይናንስ በጥልቀት መክረው ለተሻለ ስኬት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዋና ዳይሬክተር አንቶኒዮ ቪቶሪኖ በአየር ንብረት ምክንያት የሚፈጠሩ መፈናቀልን ለመግታት የተሻሻሉ የመላመድ እና የተጽዕኖ ቅነሳ ተነሳሽነት ገቢራዊ ለማድረግ በአገራት መካከል ጠንካራ አጋርነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያሰምሩበታል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ኑሯቸውን መሰረት ባደረጉ ህዝቦች ላይ አውደ-ተኮር መላመድ እና የመቋቋም አቅም ግንባታ መፍጠር ይገባል። ለዚህ ደግሞ መላመድን የሚደግፉ ፋይናንስ ለማግኘት የሚረዱ መመሪያዎች ይበልጥ የተፍታቱ መሆን ይኖርባቸዋል ሲሉ ቪቶሪኖ ይሞግታሉ። ከ 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተጓዳኝ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ (High-Level Forum) ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በሻርም ኤል ሼክ በተካሄደው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መላመድን፣ መከላከልን እና ዝግጁነትን ለማሻሻል ዓለም አቀፍ ትብብር ማጎልበት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አውስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ ያወጣቸው የስምምነት ማዕቀፎች (United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC)) በርካታ ዝርዝርና ሚዛናዊ አካሄዶችን የያዙ ናቸው። ያም ሆኖ አተገባበራቸው እዚህ ግባ የማይባል በመሆኑ የሚታሰበውን ያህል ለውጥ ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። በዚህም ቦረና ዞንን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የአየር ንብረት መዛባት፣ የሙቀትና የባህር ጠለል መጨመር፣ ጎርፍ፣ ድርቅ እንዲሁም ያልተገመቱ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። ዳሩ ግን አገራትን፣ አህጉርን፣ ዓለምን እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ግዙፍ ኩባንያዎችን ያስተሳስራል የተባለለት የአየር ንብረት ፋይናንስ በቅጡ ገቢራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች ዳፋውን ለመጋፈጥ ተገደዋል። የአየር ንብረት ፋይናንስን በመተግበር በመስኩ የተጎጂዎችን ቁጥር ሊቀንሱና የዓለምን ሥነ-ምህዳር ከተቻለ ወደ ቀድሞው ሊመልሱ አሊያም አሁን ባለበት አረጋግተው ሊያቆዩ የሚያስችሉ በርካታ አማራጮች ተግባራዊ ሊደረጉ ይገባል። ለአብነትም ለድሃ ሃገራት አርሶ አደሮች የግብርና ምርቶች ተገቢውን ዋጋ በመክፈል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን እንዲቋቋሙ ማድረግ ከአማራጮቹ መካከል አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግዙፎቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሚያስወግዷቸው በካይ ጋዞች ተመጣጣኝ የጤና ሥርዓት በመዘርጋት የታዳጊ ሃገራት ዜጎችን የጤና አገልግሎት ማሻሻል ሌላው አማራጭ ነው። የተፈጥሮ ኃብቶችን የሚጎዱ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተፈጥሮን በሚንከባከቡ ዘዴዎች መተካት እንዲሁም ብክለትን የሚያስቀሩ የምርት ሂደቶች መለማመድ ጥቂቶቹ የመፍትሄ አማራጮች ተደረገው የሚወሰዱ ናቸው። በፓሪስ ከተደረሰውን የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ 1994 ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም (Global Environment Facility-GEF) COP-16 ዓለም አቀፍ ጉባዔ በኋላ በ2010 አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund-GCF) እንዲሁም በ2001 ደግሞ ልዩ የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (Special Climate Change Fund-SCCF) እና የመላመድ ፈንድ (Adaptation Fund-AF) የተባሉ ማዕቀፎች የተዘጋጁ ቢሆንም ስለጉዳዩ የሚያስረዱ ተከታታይ ስብሰባዎች ከማዘጋጀት በዘለለ ብዙ ርቀት መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። በቅርቡ በአለም ባንክ አሰባሳቢነት በኬንያ ናይሮቢ ተዘጋጅቶ በነበረው የአህጉሪቱን መሪዎች ባለሃብቶችንና ምሁራንን ባካተተውና “One Planet Summit” በተሰኘ መሰል ጉባዔ ላይም አፍሪካውያን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚገጥማቸውን ችግሮች ተከላክለው ሁለንተናዊ ዕድገታቸውን እንዲያፋጥኑ ካስፈለገ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምጣኔ ኃብት ፖሊሲ አዘጋጅተው መተግበር እንደሚኖርባቸው መግባባት ላይ የተደረሰ ቢሆንም አሁንም ጥያቄ ያስነሳው አፈጻጸሙ ስለመሆኑ ብዙ ተብሎለታል። ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ የተባለ ድርጅት ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው አፍሪካ እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር ከ 2020 እስከ 2030 ባሉት አሥር ዓመታት 2 ነጥብ 8 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር አሊያም በየዓመቱ ከ2 መቶ ሃምሳ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን አህጉሪቱ ከዘርፉ እያገኘችው ያለው ገንዘብም ከሚያስፈልጋት 12 በመቶውን ወይም 30 ቢሊየን ዶላር ብቻ ስለመሆኑ አስነብቧል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ሊሰሩ የሚችሉ በርካታ ተግባራት እንዳሏት የሚያትተው ሪፖርቱ ከአየር ንብረት ፋይናንስ የሚገኘው ገንዘብ በትራንስፖርት፣ በኃይል ልማት፣ በኢንዱስትሪ ብሎም በግብርና፣ በአፈርና በደን ኃብት አጠቃቀም ውጤታማ በሆነ መንገድ ከዋለ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ኃብቶች መንከባከብ ከማስቻሉም ባለፈ ላቅ ያለ ፋይዳ ይኖራዋል ብሏል። ይህ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖው ያስረዳል። ላለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ገቢራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራን የማስፋፋትና የተጎዱ አካባቢዎችን የማከም ሥራ እንዲሁም አይቀሬ የሆኑትን ከተሜነትና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ታሳቢ ያደረጉ የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ለአፍሪካ ሃገራት እየፈጠረው ያለው በጎ ተጽዕኖ በግልጽ እየታየ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ጥረት ግን በአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲደገፍ አገራዊና የተቀናጀ አሕጉራዊ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል። ከአጠቃላይ የአፍሪካ አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ግብጽ ብቻ 151 ቢሊየን ዶላር ከአየር ንብረት ንብረት ፋይናንስ ማግኘት እንደሚኖርባቸው የክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ ሪፖርቱ ይገልጻል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በመጭው የCOP-28 ጉባዔ የራሷንና የአፍሪካን ፍላጎት የሚያስጠብቁ የፋይናንስ ትልሞችን የመንደፍ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ የ COP-27 ጉባዔ ለአፍሪካ ያስገኘውን ውጤት እና አንድምታ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የመሪዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አስተባባሪ በሆኑት በኬንያው ፕሬዝዳንት ሰብሳቢነት በኅብረቱ የአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ በጥልቀት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ጥረቷን የሚያጎለብት የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ጠንካራ ተሳትፎ ልታደርግ ይገባል። የአፍሪካ አገራት ገፍተው ረጅም ርቀት ያልሄዱበት የአየር ንብረት ፋይናንስ እና ሌሎች የድጋፍ አማራጮችን በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት በመጠቀም የአየር ንብረት ተጽዕኖን የሚቋቋሙበት ጠንካራ አቅም ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል። በእርግጥም አፍሪካውያን መሪዎች በሚያደርጉዋቸው ስብሰባዎች በየማዕዝናቱ በድርቅ ሳቢያ ለምግብ እጦት የተዳረጉ ህዝቦቻቸውን የሚታደጉበት ሁነኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበትን ዘዴ ነድፈው ረጅም ርቀት ሊጓዙ ይገባል። ”
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 534
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ - የአፍሪካ የዘመናት ፈተና
Feb 13, 2023 540
በረከት ሲሳይ በርካታ የአፍሪካ አገራት ነፃነታቸውን ከተቀዳጁበት ከ1960ዎቹ ጀምሮ እስካሁን እልባት ካልተገኘላቸው አፍሪካዊ ጉዳዮች መካከል ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ አንዱ ነው። ለዚሁ ጉዳይ በርካታ መነሾ ቢኖሩትም ቅኝ ግዛቱ የፈጠራቸው ፖለቲካዊ ስንጥቃቶች፣ ድህነትና ሌሎች ማኅበራዊ ምስቅልቅሎሽ ለእነዚህ የጸጥታ ችግሮች በአብዛኛው የሚነሱ ምክንያቶች ናቸው። በአህጉሪቱ ላለፉት 40 እና 50 ዓመታት መቋጫ በሌለው መልኩ እዚህም እዚያም የሚነሱ ግጭቶችና ጦርነቶች ለአያሌዎች ሞትና የአካል ጉዳተኝነት ለገሚሱ ደግሞ ለዘመናት ከኖረበት ቀዬ እንዲሰደድ ምክንያት ሆነዋል። በብዙ ጥረት የተገነቡ መሰረተ-ልማቶች ወደ ፍርስራሽነት እንዲለወጡና በሂደት ላይ ያሉ የዘመናዊ አገር ግንባታ ሂደቶች እንዲስተጓጎሉና በፈተናዎች እንዲታጀቡ አድርጓል። ይህንኑ ኢኮኖሚያዊ ኪሣራ በሚያሳይ መልኩ፤ የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ከሁለት ዓመታት በፊት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያሳየው፤ በአፍሪካ የሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች በየዓመቱ የአገራቱን አጠቃላይ አገራዊ ምርት (ጂ ዲ ፒ) እድገት ከ4 በመቶ እስከ 6 በመቶ እንዲቀንስ ያደርገዋል ይላል። በተለይም ደግሞ በኢኮኖሚው ላይ የሚከሰቱ ችግሮች ተጽዕኖ ዓመታትን የሚዘልቅ በመሆኑ ተደራራቢና ድግግሞሽ ያሏቸው ችግሮች እንዲበራከቱ በር ከፍቷል። በእነዚህ ድርብርብ ውጥንቅጦች በአህጉሪቱ በከባድ ድህነት የሚኖሩ ዜጎች ህይወት ይበልጡኑ እንዲወሳሰብባቸውና ለከፋ ማኅበራዊ ችግር እንዲጋለጡ እያደረገ ነው። ከዚህም ባለፈ የጸጥታ ችግሮች በአፍሪካ ሳያባሩ መቀጠላቸው ዛሬም ጉዳዩን በአንክሮ እንድንመለከተው ያስገድደናል። ይህንን በሚያስረግጥ መልኩ ያለፈው የፈረንጆች ዓመት (2022) ግጭቶች የተስተዋሉበት ዓመትና በዘንድሮ ዓመት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩ ተመላክቷል። በሰላም ስምምነት የተቋጨውን በኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረውን ጦርነት ጨምሮ እስካሁን እልባት ያልተገኘላቸው የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና የደቡብ ሱዳን የጸጥታ ችግሮች ተጠቃሽ መሆናቸውን ነው የአፍሪካ የደኅንነት ተቋም ሪፖርት የሚያሳየው። ከዚህ ጎን ለጎን በሳሀል፣ በቻድ ሃይቅ ሸለቆ፣ በምስራቅ አፍሪካና በሰሜን ሞዛምቢክ ጸጥታን የሚያውክ የጽንፈኝነት እንቅስቃሴ መኖሩንም አመላክቷል። ከዚህ ጎን ለጎን በቡርኪና ፋሶ፣ በጊኒ፣ ማሊ፣ ሱዳን፣ ቻድ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ጅቡቲ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ማዳጋስካርና ኒጀር የተሳካና ያልተሳካ የመፈንቅለ-መንግሥት (ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ) ሙከራ መካሄዱንና የፖለቲካ አለመረጋጋት እንደተስተዋለባቸው ነው ሪፖርቱ ያወሳው። መንግሥታዊ የአስተዳደር ግድፈቶች፣ ምርጫን ተከትሎ የሚቀሰቀስ አለመግባባትና ሌሎችም በአህጉሪቱ ላለፉት ሁለት ዓመታት የተከሰቱ የጸጥታና የደኅንነት ችግሮች ለተያዘው የፈረንጆች ዓመትም ትልቅ ሥጋት መሆኑን ነው ያነሳው። አፍሪካ ኅብረት በበርካታ አገሮች የጸጥታ ችግሮች እንዲቆሙና እንዲረጋጉ በማድረግ አዎንታዊ ሚና መጫወቱ ተገልጿል። ለአብነትም በኢትዮጵያ በዘላቂነት ግጭትን ለማቆም የተደረሰው የሰላም ስምምነት ተጠቃሽ ሲሆን በሌሎችም አገራት ወደ ተሻለ ፖለቲካዊ መረጋጋት እንዲመጡ ትልቅ ሥራ ሰርቷል። ይህም ሆኖ አሁንም ድረስ ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ በኩል በርካታ ሥራ እንደሚቀር ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ በምዕራብ ሳሀል ያለው ከአልቃይዳና ከአይ ኤስ ጋር ግንኙነት ያለው ጽንፈኛ ቡድን በአካባቢው የፈጠረው አለመረጋጋት፣ ከማሊ የፈረንሳይ ጦር መውጣትና ማሊ ራሷ ከሳሀል ቡድን አምስት የጸጥታ መዋቅር መውጣቷም ሌላው የአህጉሪቷና የአካባቢው ራስ ምታት ሆኗል። የቻድ ሃይቅ ሸለቆ አካባቢ (በኒጀር፣ ቻድ፣ በካሜሮንና ናይጄሪያ) የሚስተዋለው የቦኮሃራምና ሌሎች የጽንፈኝነት እንቅስቃሴ፣ በምስራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ራሱን ኤም23 በማለት የሚጠራው ቡድን ከማዕከላዊ መንግሥት ጋር ጦር መማዘዙ እንዲሁም በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው በመንግሥትና በተቃዋሚ መካከል የተቀሰቀሰው የሽምቅ ውጊያ አሁንም አለመቆሙ፤ የአፍሪካ ኅብረት ጸጥታን በተመለከተ በዚህ ዓመት ትኩረት ሊያደርግበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ነው የእንግሊዙ ቻም ሃውስ የተሰኘው የጥናት ተቋም መረጃ የሚያመለክተው። በተያዘው የፈረንጆች ዓመት በተለያዩ ደረጃ የሚካሄዱ 17 ብሔራዊ ምርጫ መኖራቸውንና ይህንንም ተከትሎ ሊከሰቱ የሚችሉ የድኅረ-ምርጫ ፖለቲካዊ ግጭቶችን በማስቀረት ረገድ አፍሪካ ኅብረት አዎንታዊ ሚና መጫወት እንደሚጠበቅበትም ተመላክቷል። የአፍሪካ ኅብረት ቀጣይ አቅጣጫስ? አፍሪካ ኅብረት በበርካቶች አይን ሲታይ ምንም እንኳን የፖሊሲና የስትራቴጂ ችግር ባይኖርበትም ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ በበርካታ ጉዳዮች ላይ ችግሮች ተስተውሎበታል። ለዚህም ተቋሙ ካለበት የፋይናንስና ሌሎች ተያያዥ የቴክኒክ ችግሮች በተጓዳኝ በዋነኛነት አባል አገራት በኅብረቱ ቻርተር በመመራት ረገድ በርካታ ክፍተቶች መኖራቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በተለይም በጸጥታና ደኅንነት ምክር ቤት በኩል የሚወስናቸው ስምምነቶች ገቢራዊ አለመሆናቸው ትልቅ ክፍተት ሲሆን ምክር ቤቱም በቅርቡ ያደረገው ስብሰባ ይህንኑ አጋልጧል። ይህም አፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ መልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ እንዲጎለብት በማድረግ ረገድ ያለው ቁርጠኝነት ልዩ ትኩረት የሚሻ መሆኑን አመላክቷል። ለአብነትም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2020 የጥይት ድምፅ የማይሰማባት አህጉር ለመፍጠር ያቀደው ዕቅድ ምንም እንኳን ዕቅዱ ከጅምሩም ቢሆን ያለው ነባራዊ ሁኔታና የግጭቶች የመስፋፋት አዝማሚያ ከግምት በማስገባት ሊሳካ እንደማይችል በርካታ የመስኩ ተንታኞች ቢናገሩም ኅብረቱ በዚህ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት አልቻለም። ለዚህም ደግሞ በቀዳሚነት ምንም እንኳን የአባል አገራት የፖለቲካ ቁርጠኝነት ማነስ ትልቁን ድርሻ ቢይዝም የሚወስዳቸው እርምጃዎች ሳይሸራረፉ ተግባራዊ ለማድረግ መቸገሩን ነው የሚያሳዩት። በአፍሪካ በሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ሥራዎች በቁርጠኝነት መሥራት ይገባል። በተለይም ደግሞ አፍሪካ ኅብረት በቅርቡ ዳግም የከለሰውን በአህጉሪቱ የጥይት ድምፅ ለማጥፋት የወጣውን ፍኖተ- ካርታና እንዲሁም የክትትልና የግምገማ ማዕቀፍ ፈጥኖ ወደ ሥራ ማስገባት ይኖርበታል። ይህንንም ተከትሎ በጸጥታና የደኅንነት ምክር ቤቱ ያቋቋመውን የባለሙያዎች ቡድን የያዘ ማዕቀብ ለመጣል የሚሰራው ንዑስ ኮሚቴም በአግባቡ መጠቀም አለበት። አሁን ላይ በአህጉሪቱ ለጸጥታ መስፈን ሥጋት በሚሆኑና በሚያቆጠቁጡ ጉዳዮች ላይ እልባት ለመስጠት መረባረብ እንዳለበት ነው የሚጠቀሰው። በተመሳሳይ የሚወስዳቸው እርምጃዎችም በባህሪያቸው ተከታታይነትና ወጥነት ያላቸው እንዲሁም ችግሮች ከተፈጠሩ በኋላ ሳይሆን ከመፈጠራቸው በፊት አስቀድሞ መከላከልና ማክሸፍ ላይ ሊረባረብ እንደሚገባ ነው የሚያነሱት። ከዚህ በተጓዳኝ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማፋጠን የሚያስችሉ የአገራትን የፖለቲካ እንቅስቃሴ መደገፍና በዘላቂነት ዴሞክራሲ ባህል እንዲሆን የሚያስችሉ ሥራዎችን መደገፍ እንዳለበትም ነው የሚነሳው። በተለይም ደግሞ ወጣቶችን ያሳተፉ የዴሞክራሲ ግንባታ ሥራዎች በስፋት መሠራት እንዳለበት ነው የሚጠቀሱት። ከዚህ ጎን ለጎንም የአፍሪካ የእርስ በርስ መገማገሚያ መድረክም (ፒር ሪቪው ሜካኒዝም) በተለይም መልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲጎለብት በማድረግ ረገድም አበርክቶው ከፍ እንዲል መሠራት ይጠይቃል። የሰላም ሥራውን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችለውን የሰላም ፈንድም ማሰባሰብ እንዳለበትም ነው የሚነሳው። ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት አጋማሽ ላይ የሰላም ፈንዱ አጠቃላይ ገቢ 328 ሚሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 22 አባል አገራት ሙሉ በሙሉ እንዲሁም አምስት አገራት ደግሞ በከፊል የሚጠበቅባቸውን መዋጮ አዋጥተዋል። በሌላ በኩል 28 አባል አገራት ደግሞ መዋጮውን መክፈል አለመቻላቸውን ነው የአፍሪካ ኅብረት የሰላምና ደኅንነት ሪፖርት የሚያመለክተው። በመሆኑም አፍሪካ ኅብረት አባል አገራት የሚያዋጡትን ገንዘብ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጨርሱ ቅስቀሳ ማድረግን በአፍሪካ ጥላ ሥር በተለያዩ አገራት የሚያንቀሳቅሰውን የሰላም ሥራ ውጤታማ ማድረግ ይገባዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(ተ.መ.ድ) የጸጥታ ምክር ቤት ጉዳይ ላለፉት 15 ዓመታት በአፍሪካ መሪዎች በስፋት የተቀነቀነው አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት ይገባል የሚለው ጉዳይም አፍሪካ ኅብረት በዘንድሮ ጉባዔው ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። ምክር ቤቱ ከሚመለከታቸው ጉዳዮች ውስጥ ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑት አፍሪካን የተመለከቱ መሆናቸውና ይህም ሆኖ በምክር ቤቱ ውስጥ አፍሪካ አለመወከሏ የፍትሃዊነት ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል። በርካታ የአፍሪካ መሪዎች እንዲሁም ኅብረቱን በሊቀ-መንበርነት የመሩት እስከ ወቅቱ ሊቀ-መንበር የሴኔጋሉ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል ድረስ ጥሪያቸውን በተለያዩ መድረኮች አሰምተዋል። አሁን አሁን ላይም ጥያቄውን ምንም እንኳን የሩቅ ምስራቆቹ ጃፓንና ቻይና እንዲሁም ሕንድ አስቀድመው ቢቀበሉትም በተለይም አንዳንድ የምዕራብ አገራት ያሏቸውን የሃሳብ እቀባ በማንሳት ጉዳዩን እንዲጋሩት በማድረግ አፍሪካ ትልቅ ስኬት አግኝታለች። ይህም ሆኖ አሁንም አፍሪካ ስንት መቀመጫ ይኑራት? እንዲሁም ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ይሰጣት ወይስ አይሰጣት? የሚለው ጉዳይ ላይ ክርክሮቹ እንደቀጠሉ ነው። በዘንድሮ ጉባዔው ኅብረቱ በእነዚህ ጉዳይ ላይ ተወያይቶ ወደ መጨረሻ ምዕራፍ ላይ የሚደረስበትን ውሳኔ ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል። ይህንንም ማድረግ ከተቻለ በአፍሪካ ቀደምት መሪዎች ሲቀነቀን የቆየውን "አፍሪካዊ መፍትሔ ለአፍሪካ ችግሮች" የሚለውን ብሂል እውን ለማድረግና አህጉሪቷ ላይ ዘላቂ ሰላምና ደኅንነትን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ላይ አዎንታዊ አበርክቶ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
ጠንካራ አንድነት - ለዘላቂ ሰላም መሰረት!
Feb 3, 2023 486
በእንግዳው ከፍያለው (ባህር ዳር ኢዜአ) በረጅም እንጨት ጫፍና ጫፍ በገመድ ታስረው የተንጠለጠሉ ቋጠሮዎችን ተሸክማ ከጓደኞቿ ጋር ገበያ እየሄደች ነበር የተገናኘነው። ወጣት ማሪማ ሜካ ትባላለች፤ ዕድሜዋ ከሃያ ዓመት አያልፍም። በእንጨቱ አንደኛው ጫፍ 10 ሊትር አረቄ የያዘ ጀሪካን፤ በሌላኛው ጫፍ ደግሞ ሌላ ቋጠሮ በማንጠልጠል ተሸክማለች። ሸክሙን በትካሸዋ ላይ ጣል እድርጋ ፈጠን እያለች ስትራመድ ላየ በፊቷ ላይ አንዳች የብርታትና የጽናት መንፈስን ያነባል። እንደእኔ ለአካባቢው እንግዳ የሆነ ሰው “ሴት ልጅ እንዴት ይህን ያህል ክብደት ተሸክማ ትጓዛለች?” ብሎ ራሱን ሊጠይቅ ይችላል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማንዱራ ወረዳ ነዋሪዋ ወጣት ማሪማ ግን ሸክሙ እንደ ኩበት ቀሏት ይሁን ጽናቱን ፈጣሪ ሰጥቷት ባላውቅም በደስታ ወደ ፊት መራመዷን ቀጥላለች። “የኛ ችግር የምንይዘው ሸክም ሳይሆን የጸጥታ ስጋት ነበር” የምትለው ወጣቷ ባለፉት ዓመታት በኛ ላይ የደረሰው አስከፊ ሰቆቃና መከራ ለጠላትም እንዲገጥመው አልመኝም በማለት ትናገራለች። ባለፉት ዓመታት በአማራና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አዋሳኝ ወረዳዎች ሲከሰት የነበረው ግጭት የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች ለሞት፣ ለስደት፣ ለንብረት መውደም እንዲሁም ለተለያዩ ችግሮች ዳርጓቸው መቆየቱ የቅርብ ትውስታ ነው። አካባቢው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚገነባበት፣ ሰፋፊ የእርሻ ኢንቨስትመንት፣ የስኳር ፕሮጀክቶችና ሌሎች የኢንዱስትሪ ልማቶች ያሉበትና ለመተግበር የታቀደበት በመሆኑ የውጭ ሃይሎች ግጭት እንዲነሳ እጃቸውን ሊያስገቡ እንደሚፈልጉ ሳይታለም የተፈታ ነው። ወጣት ማሪማ ግጭት በተከሰተባቸው በነዚያ አስከፊ ጊዜያት የነበረውን ሁኔታ፣ የደረሰውን ጉዳት፣ በተከፈለው መስዋዕትነት የመጣውን ሰላም በሚያስታውስ የተስፋ ስሜት "ጸረ ሰላም ሃይሎች ያስነሱት ግጭት ለዘመናት በአንድነት የኖረውን የሁለቱ ክልሎች ህዝቦች ተስፋ አጨልሞት ነበር፤ በሰላም እጦት ሁሉም ህዝብ ጫካ ገብቶ ኑሮውን ከዱር አውሬ ጋር ያደረገበት የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው" ትላለች። በአሁኑ ወቅት ጸረ ሰላም ሃይሎችና ተባባሪዎቻቸው የፈጠሩት ሰው ሰራሽ ችግር ሊፈታ መቻሉ እፎይታን መፍጠሩን ትገልጻለች። በወቅቱ ሕክምና፣ መድሃኒትና ሌሎች የጤና መጠበቂያ ቁሶች ባለመኖራቸው ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በወባ እና ሌሎች በሽታዎች ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች እንዳሉ በመጥቀስ፤ በአሁኑ ወቅት የጸጥታ አካላትና ሰላም ፈላጊ የአካባቢው ተወላጆች ከመንግሰት ጋር በመሆን ባደረጉት ጥረት የነበረው ግጭት ተወግዶ በአካባቢው ሰላም ሰፍኗል። ይህም ለማሪማና ለአካባቢው ነዋሪዎች እፎይታን በማጎናጸፉ በጣም ደስተኛ ናቸው። የተገኘውን ሰላም ተከትሎ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማንዱራ ወረዳ ተነስታ በአማራ ክልል አዊ ዞን ቻግኒ ከተማ በመምጣት ለመገበያየት በቅታለች። ከጓደኞቿ ጋር ከቻግኒ ከተማ የሚፈልጉትን ገዝተው ወደ አካባቢያቸው ወስደው በትርፍ ለመሸጥ ምቹ ሁኔታም ተፈጥሮላቸዋል። በቻግኒ ከተማ የቅዳሜ ገበያ የተለያዩ የንግድ እንቅስቃሴዎች ይካሄዳሉ። በርበሬ፣ የተለያዩ የጥራጥሬ፣ የቅባትና የአገዳ ምርቶች ለሽያጭ ይቀርባሉ። አልባሳት፣ የሴቶች ጌጣጌጥ እና የንጽህና መጠበቂያ ቁሶች እንዲሁም ሌሎች የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ንግድ ልወውጥ የሚካሄድባት ከተማ መሆኗን በነበረኝ የአጭር ጊዜ ቆይታ አስተውያለሁ። ገበያተኛው የተፈጠረውን ሰላም በማጣጣም ላይ መሆኑን በገበያው ውስጥ ከሚያሳየው መስተጋብር መረዳት ቀላል ነው። እኔም ይሄን በተደጋጋሚ ታዝቢያለሁ። ከህዝቡ ፊት ያነበብኩት በግጭቱ የተነሳ በደረሰው ችግር ምክንያት ቁርሾና ቂም በቀል ውስጥ መግባትን ሳይሆን የሰላምና እርስ በርስ መዋደድና የመደጋገፍ ስሜትን ነው። ይሄን ደግሞ በቻግኒ ከተማ በሚካሄደው የቅዳሜ ገበያ መስተጋብር ላይ ተገኝቶ ማረጋገጥ ይቻላል። ገበያው የሁለቱም ክልሎች ህዝቦች ያላቸውን ይዘው መጥተው በነጻነት የሚገበያዩበት ነው። አሁን በሰላም ተገበያይቶ ወደ ቤት የሚመለስበት ሁኔታ በመፈጠሩ ለወጣት ማሪማ እና እንደ እሷ ላሉ ወጣቶች ደስታና እፎይታን ሰጥቷል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የማንዱራ ሚሊሻ የሆኑት አንመይ አልቤም በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም መታጣት ችግር ዛሬ መፈታት በመቻሉ በነጻነት ያለስጋት ለመገበያየት መብቃቱን አስረድቷል። "ያ አሰቃቂና የእልቂት ጊዜ አልፎ ተገናኝተንና እርስ በርስ ተገበያይተን በሰላም ወደየቤታችን እንመለሳለን ብሎ ማሰብ እንደ ከንቱ ህልም ነበር" ይላል የነበረውን ሁኔታ ሲያስታውስ። “ሚሊሻ እንደመሆኔ ከፌዴራልና ከክልሎች የጸጥታ ሃይሎች ጎን በመሰለፍ ግጭት ቀስቃሾችን ለመፋለም ጨካ ለጫካ ያሳለፍነው ጊዜ መቼም አይረሳኝም” ያለው ሚሊሻ አንመይ፣ ስንቶች በሕክምና፣ በመድሃኒትና ምግብ እጦት ህይወታቸው ማለፉን አንስቷል። "አማሟቴን አሳምረው" እንደሚባላው በወጉ መሞትና መቅበር ትልቅ ጸጋ መሆኑን የገለጸው አንዳች የሀዘን ስሜት ውስጥ በመግባት ነው። አሁን ላይ ሁሉም የደረሰውን ጉዳት በመርሳት የተገኘውን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል እየተንቀሳቀሰ ነው። የሁለቱ ክልል ህዝቦች ቂም በቀልን ትተን በጋራ የምንሰራበት ወቅት ላይ መድረሳችን ህዝቡ ከጥንት ጀምሮ ያለው የመተሳሰብ፣ የአብሮነትና አንድነት የመንፈሰ ጠንካራነት ማሳያ እንደሆነም ነው የገለጸው። በእርግጥም የማንዱራ ሚሊሻው እንዳለው በአካባቢያቸው ትምህርት ቤቶች በመከፈታቸው ህጻናት ያለስጋት በመማር ላይ ናቸው። የጤና ተቋማትም የተለመደውን የሕክምና አገልግሎት እየሰጡ ነው። በሰላም እጦት ተዘግተው የነበሩ መንገዶች በመከፈታቸውም ሁሉም ተሯሩጦ ኑሮውን ለማሸነፍ ላይ ታች እያለ ነው። ባለሃብቶችም በክረምቱ በግብርናው መስክ ተሰማርተው ማልማት ችለዋል። የጸጥታ ስጋት ተወግዶ ሌሎች የልማት ሥራዎች ሲተገበሩ ማየት ትልቅ ስኬት ነው። በአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የቻግኒ ከተማ ነዋሪ አቶ ሲራጅ አዲስ እንዳሉት ግጭት በነበረበት ወቅት በአካባቢው የኢንቨስትመንትና የንግድ እንቅስቃሴ ተዳክሞ ነበር። እሱ ቀርቶ በሰላም ውሎ ለማደር ጊዜው ከባድ ነበር ይላሉ። "የተገኘው ሰላም በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች እና በህብረተሰቡ የጋራ ጥረት በመሆኑ ሰላሙ አስተማማኝና ዘላቂ እንዲሆን ሁላችንም የበኩላችንን መወጣት ይኖርብናል" ብለዋል። አሁን ላይ ያለፈውን የመከራ ጊዜ፣ በሞት የተለየውን ወገን፣ የወደመውን ሀብትና ንብረት በመርሳት በተገኘው ሰላም በጋራ ሰርቶ ራስንና አካባቢውን ለመለወጥ መትጋት እንደሚገባ ነው የመከሩት። ያለፈን በደልና ቅሬታ በእርቅና በይቅርታ በማለፍ ነገን ብሩህ ለማድረግ መትጋት አለብን በማለትም ነው ያስገነዘቡት። አቶ ሲራጅ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት የጉሙዝ ማህበረሰብ ወደ ቻግኒ መጥቶ ያለውን ሽጦ የሚፈልገውንም ገዝቶ ይሄዳል፤ እነሱም ወደ መተከልና ማንዱራ በመሄድ ያላቸውን ይሸጣሉ፤ የፈለጉትንም ገዝተው የሚመጡበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። ይሄን አብሮነት በማጠናከር ሁለንተናዊ የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰላምን ማጽናት ላይ ጠንክሮ መስራት ይገባል። በአማራም ሆነ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ችግር ሲፈጥሩ የነበሩ ወንጀለኞችን አጋልጦ ለህግ ማቅረብ ያስፈልጋል። አሁንም የጥፋት ተልዕኮ ይዘው ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱትን አደብ እንዲገዙ ማድረግ ተገቢ ነው። ወንጀለኛን ለህግ አጋልጦ መስጠትን ከተለማመድን ነገም አካባቢውን የጦር ቀጣና ለማድረግ የሚፈልጉ የጥፋት ሃይሎች መግቢያ ቀደዳ አይኖራቸውም ይላሉ። ሃገር በአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን በሁሉም ዜጎች የተባበረ ክንድ ትገነባለች፤ ደህንነቷም ድንበሯም ይጠበቃል። ለዛሬው ትውልድ የደረሰችውም የብዙዎች ዋጋ ተከፍሎባት እንደመሆኑ በጋራ በሰላምና በአብሮነት ይሄንኑ ማስቀጠል የግድ ይላል። በተለይም የሰላም ጉዳይ ቅድሚያ ትኩረት የሚወስድ እንደመሆኑ አካበቢን የመጠበቅ የነቃ ተሳትፎን ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ ልታለማውና ልትጠቀምበት የምትችለው ገና ብዙ ያልሰራችበት ሃብት ባለቤት መሆኗ የአንዳንድ ሃይሎችን ቀልብ መሳቡ የሚጠበቅ ነው። ሰላሟ ሲረጋገጥ የዜጎች ደህንነት ሲከበር የተጀመረው የእድገት ጉዞ መፋጠኑ የማይቀር በመሆኑ ሁሉም የድርሻውን መወጣት ይኖርበታል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 97
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 279
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት። እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 410
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል። “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 587
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
መጣጥፍ
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 545
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ)
Jan 25, 2023 587
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ) አየለ ያረጋል (ኢዜአ) መዳረሻዬ ሽሬ እንዳስላሴ ነው። ለዘገባ ሥራ ከባህርዳር- ጎንደር- ደባርቅ- ሸሬ መንገድ ከሚዲያ ባልደረቦች ጋር እየተጓዝኩ ነው። የጥምቀት ሙሽራዋ ጎንደር እየተኳኳለች ነበር። ደባርቅ ከመድረሴ በፊት ዳባት ትገኛለች-የደጃች አያሌው ብሩ ቁርቁር ከተማ። ደጃች አያሌው ትውልዳቸው በጌምድር ጋይንት ቢሆንም ግዛታቸውና ኑሯቸው ዳባት ነበር። ሞገደኛው ደጃዝማች አያሌው ብሩ በጎንደር ማኅበረሰብ ዘንድ ዝናቸው የናኘ ነው። ደጃዝማች አያሌው በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ (ከልጅ ኢያሱ እስከ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ-መንግሥት) ታሪካዊ ክንውኖች ጉልህ ተሳትፎ አላቸው። አንዷን ብቻ ልምዘዝ። ራስ ተፈሪ ‘ንጉሠ-ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ’ ደጃች አያሌው የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ ጉግሳ ወሌ ብጡልን (የንግሥት ዘውዲቱን ባለቤት) ወግተው የጎንደር ግዛት ‘ራስ’ ተብለው ለመሾም ቃል ቢገባላቸውም፤ ተልዕኳቸውን ተወጥተው ቃሉ ባለመፈጸሙ ደጃዝማቹ ከአጼው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። በዚህም:- "አያሌው ሞኙ፣ ሰው አማኙ ሰው አማኙ፣ የአያል ጠመንጃ፣ ስሟን እንጃ ስሟን እንጃ…” በማለት የጎንደር አዝማሪ አዚሟል። ዛሬም ይህ ግጥም የብዙ ባህላዊ ዘፈኖች አዝማች ነው። ደጃች አያሌው ብሩ ደፋር ናቸው ይባላል። ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር ቢቀያየሙም በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ሲመጣ ቅድሚያ ለአገሬ ብለዋል። ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘው የዶክተር ሀራልድ ናይስተሮም (ትርጉም ገበየሁ ተፈሪ እና ደሳለኝ አለሙ) መጽሐፍ እንደተጠቀሰው ደጃች አያሌው “ንጉሡ እንደኛ ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሁላችንም ናት" ብለው ጦራቸውን መርተው በሽሬ ግንባር ዘምተዋል። ጉዟችን ቀጥሏል። ደባትን እያለፍን ነው። ‘እንኳን ደህና መጡ፤ ወደ ጭና ታሪካዊቷ ሥፍራ’ የምትለዋን ታፔላን በስተግራ እያየን ወደ ደባርቅ ገሰገስን። የሰሜን ተራሮች የብርድ ወጨፎ ያረሰረሳትን ደባርቅን ከማለፋችን ሊማሊሞ ጠመዝማዛ ቁልቁለት ተቀበለን። አስፈሪ የሊማሊሞ መልክዓ ምድር የደጋው ሰሜን ውርጭ እና የተከዜ በርሃ ኬላ ነው። ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህን “የሰማይ የምድሩ ኬላ፣ የየብስ የጠፈሩ ዋልታ አይበገር የዐለት ጣራ፣ አይመክተው መከታ ሊማ-ሊሞ አድማስ ሰበሩ፣ በጎማ ፈለግ ይፈታ? በትሬንታ እግር ይረታ?…” ብሎ የመኪና መንገድ ተገንብቶበት በማየቱ ግርምቱን የተቀኘለትም ለዚህ ይመስላል። ከሊማሊሞ ቁልቁለት በኋላ አዲ-አርቃይ፣ ዛሪማ፣ ማይፀብሪ እና ሌሎች የጠለምት ወረዳ ከተማዎችን አልፈን፤ የዋልድባ ረባዳማ አካባቢዎችን ተሻግረን ተከዜ ወንዝ ደረስን። የዚህን መንገድ እና ተከዜ ወንዝን ሳስብ የሀዲስ ዓለማየሁ ትዝታ አስተከዘኝ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር የወገንን ጦር ፊት ለፊት መቋቋም ሲሳነው በሰው ልጆች ላይ ተደርጎ የማያውቅ መርዝ በጅምላ የፈጀበት አሳዛኝ ታሪክ ነበር። በተከዜ ወንዝ ውሃን በመመረዝ የወገን ጦር ያለቀበት ሥፍራ ነው። የተከዜ ሸለቆ በኢትዮጵያዊያን ደምና አጥንት ዋጋ የተከፈለበት ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በአንድ ዕለት የተመለከቱትን እንዲህ ጽፈውታል። “የተከዜ ውሀ እመሻገሪያው ላይ ሰፊና ፀጥ ያለ ነው። ታዲያ ያ ሰፊ ውሀ፤ ገና ከሩቅ ሲያዩት ቀይ ቀለም በከባዱ የተበጠበጠ ይመስላል። “ምን ነገር ነው፤ ምን ጉድ ነው?” እየተባባልን ቀረብ ስንል መሻገሪያው በቁሙም በወርዱም ከዳር እስከ ዳር ሬሳ ሞልቶበት የዚያ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው። የሰው ሬሳ፣ የፈረስ እና የበቅሎ ሬሳ፣ ያህያ ሬሳ፣ ያውሬ ሬሳ፥ ሬሳ ብቻ! እግር ከራስ ራስ ከእግር እየተመሰቃቀለ እየተደራረበ ሞልቶበት፥ የዚያ ሁሉ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው”። ይሉናል። ቀጥለውም “በእውነቱ እንዲህ ያለውን መሳሪያ ምንም ጠላት ቢሆን በሰው ላይ ለማዋል የሚጨክን ሰው፥ ሰብዓዊ ስሜት የሌለው፣ አለት ድንጋይ የተፈጠረበት መሆን አለበት፤ እንዲህ ያለውን መሳሪያ በሰው ላይ ማዋል ሰብዓዊ ህሊና ሊሸከመው የማይችል እጅግ ከባድ መሆኑን ዓለም ሁሉ ያወቀውና ያወገዘው በመሆኑ የኢጣሊያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ከማድረጉ በቀር “ሌላ መንግሥት በሌላ አገር ላይ አደረገ’ ሲባል ተሰምቶ የሚያውቅ አይመስለኝም” ብለዋል። ከተከዜ ባህር ማዶ ጉዞዬ ያገኘኋት ሌላዋ ታሪካዊ ሥፍራ እንዳባጉና ናት። እንዳባጉና የወገን ጦር ትልቅ ገድል የፈጸመበት ነው። ጀግኖች አባቶቻችን የጠላት ታንክ ሳያስፈራቸው የጠላት ጅምላ ጨራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ተቋቁመው ጠላትን ድባቅ የመቱበት፤ ወደ አክሱም እንዲያፈገፍግ ያደረጉበት ሥፍራ ነው። “የጠላት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በጦር ሜዳው ትንንሽ ቦምቦች አውቶማቲክ ጠመንጃ ይተኩስ ነበር። አቢሲኒያኖች ደግሞ ከጠላት ጋር ግብግብ ገጥመው ጉዳይም አልሰጡትም ነበር…” ይላል ዶክተር ሀራልድ ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘ መጽሐፉ። ይህ አካባቢ በሀገር ፍቅር የነደዱ ኢትዮጵያዊያን ደም ያፈሰሱበት፣ አጥንት የከሰከሱበት፤ ለኢትዮጵያ መስዕዋትነት የከፈሉበት ነው። ይህ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ቀጣና ነው። ቀኑ ተገባዷል። ጉዟችን እንደቀጠለ ነው። እኔም የማሽላ ማሳዎችን ግራ ቀኝ እየተመለከትኩ ለዕለቱ መዳረሻችን ወደሆነችው ሽሬ ከተማ ገባን። ሽሬ በትግርኛ ‘ሽረ’ ሲሉት ይደመጣሉ። በእርግጥ ሽሬን ለመጀመሪያ ጊዜ መርገጤ ነው። ዕለቱም ጥር ሥላሴ ነው። ሽሬ በጥር ሥላሴ ትደምቃለች፤ ሙሉ ስሟም ሽረ እንዳስላሴ ነው። የሽሬ ሥላሴ ጠበል ሽሬ ደርሰን ማረፊያችንን ያዝን። ጊዜው በጣም አልመሸምና ከተማዋን በቀላሉ መቃኘት ይቻላል። ሽሬ ሰፊና ደማቅ የዞን ከተማ ናት። ከመካከላችን የአንደኛው ባለሙያ ቤተሰቦች ሽሬ ነበሩና አስጠሩን። ለሥላሴ ጠበል ግብዣ። ባል እና ሚስቱ ከልክ በላይ መስተንግዶ አደረጉልን። ‘ጠብ እርግፍ አድርገው አስተናገዱን’ ማለት ይቀላል። እንግዳ መቀበል ነባር ኢትዮጵያዊ እሴታችን ቢሆንም ጦርነት ውስጥ ለቆየ አካባቢ የተለየ መልክ ነበረው። እንግዳ አቀባበላቸው በእርግጥም የመሃል አገር ሰው የናፈቃቸው ይመስላል። የተትረፈረፈ እህልና ውሃ አቅርበው በ’ብሉልን፤ ጠጡልን’ ተማጽኗቸው የተነፋፈቀ ቤተ-ዘመድ ግብዣ አስመሰሉት። የሥላሴው ጠበል የሸሬ ጠላ ቀረበ። የሸሬ ጠላ ሳስታውስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ታወሱኝ። የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምሀሩ ፕሮፌሰር ሽብሩ በዘመነ ደርግ በዕድገት በሕብረት ዘመቻ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ሽሬ ዘምተው ነበር። በወቅቱ ታዲያ የሸሬ ጠላ ፍቅር ይዟቸው በየጊዜው ሲኮመኩሙ የተመለከቱ ሰዎች ‘ፕሮፌሰሩ ከጠፉ የሚገኙት ጠላ ቤት ነው’ ሲባሉ እንደነበር ‘ከጉሬ ማርያም እስከ አዲስ አበባ’ በተሰኘው ግለ ታሪካቸው አስፍረዋል። ከግብዣ መልስ ከማረፊያ ሆቴል ላይ ሆኜ ከተማዋን ስቃኛት ከጦርነት ድባቴ የተላቀቀች ይመስላል። የአመሻሽ ሕዝቡ እንቅስቃሴም ሆነ እስከ ሌሊቱ አጋማሽ የሚሰሙ የመዝናኛ ቤቶች ሙዚቃዎች የከተማዋን አሁናዊ መልክ የገለጠልኝ ነበር። ንጋት ላይ በቁርስና ቡና ሰዓታት ከሰዎች ጋር መስተጋብሬ ጀመረ። በጦርነት አዙሪት የከረመችው ሽሬና አካባቢው ኑሮ እጅጉን የከበደ ነበር። መልከ-ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች አስተናግደዋል። አሁናዊ ምላሻቸው “ተመስገን፤ ያ ሁሉ አለፈ” የሚል ነው። ገበያው ተረጋግቷል፤ ማህበራዊ ኑሮ ተመልሷል። ድህረ-ሰላም ስምምነት ለሽሬ ነዋሪዎች ሁለንተናዊ እፎይታን አንብሯል። ከቀናት በኋላ በአክሱም የታዘብኩትም እንዲህ ነው። ኑሮን ያቀለለው የተቋማት አገልግሎት ጅማሮ በመጀመሪያ ዘገባ ስራዬ መሰረተ ልማትን አገልግሎት ቃኘሁ። ባንክ፣ ቴሌ፣ ሆስፒታል… መሰሎቹን። ተጠቃሚዎችንም፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ስራ ሃላፊዎችንም አነጋገርሁ። ከሰላም ስምምነቱ ማግስት ጀመሮ ተቋማቱ ወደስራ መመለሳቸው ከሁለንተናዊ ችግር እንደታደጋቸው ያነሳሉ። በትራንስፖርት እየተንቀሳቀሱ፣ በኤሌክተሪክ ስራዎቻቸውን እየከወኑ ነው። ለሁለት ዓመታት የተቋረጠው አገልግሎት አቅርቦት እና የአገልግሎት ፈላጊዎች ፍላጎት ግን አሁንም ሙሉ በሙሉ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ የተጠቃሚዎችም፤ የአገልግሎት ሰጭዎችም ሀሳብ ነው። በሽሬ ስሁል ሆስፒታል የተመለከትኳቸው፤ ያነጋገርኳቸው፤ ከታዳጊዎች እስከ አዛውንት ዕድሜ ያሉ ህሙማን የሰላም አየር ማግኘታቸው የሕይወታቸው ዑደት እንዲቀጥል አድርጓል። ድንገተኛም ሆነ ነባር ህመም ያለባቸው ሰዎች በነጻ እየታከሙ ነው ያገኘኋቸው። ሰላም ከሌለ መታከም ቀርቶ በቅጡ ማስታመም፤ በወጉ መቀበርም እንደማይቻል ገልጸውልናል። የጤና፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት የግብዓት ክፍተቶች የማሟላት ሰራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም በፌዴራል ደረጃ በየተቋማቱ የተመደቡ አስተባባሪዎች አረጋግጠውልኛል። የጸጥታ አካሉና የህብረተሰቡ ትብብርም የሚያስቀና እንደሆነ ግለሰቦችም፤ የጸጥታ አካላትም ነግረውኛል። አክሱም ጺዮን ማርያም፣ ሽሬ ስላሴ ንግስ፣ የጥምቀት በዓላት ከሶስት ዓመታት በኋላ በአደባባይ ታቦት ወጥቶ ተከብሯል። የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮችም ይህንኑ ነው ያረጋገጡልኝ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት ቤተሰባዊ የሆኑ ይመስላል። እንቅስቃሴያቸውም የሰላማዊ ቀጠና መልክ ያለው ነው፤ ዩኒፎርም ከመልበሳቸው በስተቀር ጀሌያቸውን ይንቀሳቀሳሉ። ይህ ደግሞ መተማመን ከመፍጠር ባለፈ ጦርነት ውስጥ ለቆየ ማህበረሰብ ከስነ ልቦና ጫና እንዲላቀቅ አይነተኛ ሚና እንደላው ይሰማኛል። ኢ-መደበኛ የሽሬና አክሱም ወጎች ያረፍኩበት ሆቴል ባለቤት ‘አደይ’ ተግባቢ ናቸው። ደግ እናት ይመስላሉ። ከገባን ጀምሮ ‘ጠላ ተጎንጩ፤ ቡና ጠጡ’ ጭንቃቸው ነው። ሁለት ቀን ቡና አስፈልተውልናል፤ ጠላ አቅርበው ዘክረውናል። ይህ ሁሉ ሲሆንም ለከተማው እንግዳ መሆናችንን እንጂ ስለሙያችንም ሆነ ስለሌላ ማንነታችን አያውቁም ነበር። ብዙ መጨዋወትና ውሎ አዳር በኋላ ነው ጋዜጠኛ ስለመሆናችን ያወቁት። አደይ ተጨዋች ናቸው። አማርኛ ያዝ ቢያደርጋቸውም ጨዋታቸው ‘ኩርሽም’ ነው- ተሰምቶ የማይሰለች። በአጋጣሚ ‘ሰለክላካ’ ስለምትባለዋ ታሪካዊ ሥፍራ ጠይቄያቸው እያወጋን ነበር። ‘እንደእናንተ ወጣቶች ሳለን ‘ሰለክላካን ያላዬ ሸዋን ያመሰግናል’ ይባል ነበር። ታዲያ አንድ የሸዋ ሰው መጣና ሰለክላካን አየና ‘በቃ ይቺ ናት’ ሰለክላካ’ ብሎ ተገረመ” ብለው አሳቁን። (የፍቅር እስከ መቃብር መሪ ገጸ-ባህሪው ‘በዛብህ’ ወደ ዲማ ጊዮርጊስ ሄዶ ‘የዲማ መልኳ እና ዝናዋ’ ተጣርሶበት እንደተገረመበት ቅጽበት መሆኑ ነው)። አደይ የተጀመረው ሰላም ፍጹም ምሉዕ ሆኖ ወደ ቀደመ ኢትዮጵያዊ መልካችን የምንመለስበት ጊዜ እንዲመጣ ይሻሉ። ከጦር-ነት ወደ ሰላም-ነት! ቆንጂዬዋ ፊዮሪ የኮሌጅ ተማሪ ነበረች። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጀምሮ በኋላም በጦርነት ሳቢያ ትምህርቷን ካቆመች ሦስት ዓመታት ሆኗታል። ጦርነቱ ከቆመ በኋላ የጀበና ቡና ጀምራለች። ደንበኞቿ ሰብሰብ ብለን እንቀመጣለን። ፊዮሪ ከስኒ ማቅረቢያዋ ላይ አነስተኛ ጀበናዋን፤ የሚያማምሩ ስኒዎቿን እና መዓዛው ከሚያውድ የዕጣን ማጨሻዋ ጋር ሰድራ ይዛ ትቀርባለች። ከመካከላችን ካለው ጠረጴዛ ላይ ታስቀምጥና እርሷም ወንበር ይዛ ከመካከላችን ትቀመጣለች። ቡናው እስኪሰክን ጨዋታዋን ታስኮመኩመናለች። ቡናው ከሰከነ በኋላ ቡናዋን ቀድታ ለእያንዳንዳችን በእጃችን እያነሳች ትሰጣለች። በሽሬ ቡና የሚቀርበው በዚህ መልክ ነው። ለፊዮሪ እና መሰሎቿ ጦርነቱ ክፉ ጠባሳ መጣሉ፤ ተስፋቸው ላይ መጥፎ አሻራ ማስቀመጡን ታነሳለች። አሁን ግን ብሩህ ተስፋ ሰንቃለች። ስለነገዋም “ሰላሙ ይዝለቅልን፤ ትምህርቴን ለመቀጠል እመኛለሁ” ትላለች። አክሱም ከሽሬ በስተሰሜን 60 ኪሎ ሜትር ይርቃል። ከሽሬ አክሱም ስንንቀሳቀስ ከጥምቀት ዕለት በስተቀር ገበሬው የግብርና ሥራዎቹን እየከወነ ነበር። አርሶ አደሩ ያርሳል፤ መስኖውን ያለማል። የተዘራውን ውሃ ያጠጣል። የበቀለ ቡቃያውን ይኮተኩታል። ከጦርነት ወደ ልማት መዞሩን ዐይኔ ታዝቧል። በጥምቀት ዋዜማ፤ የከተራ በዓል ዕለት ሁለት ጎራማይሌ የረፋድ ትዕይንቶችን ላንሳ። ከአክሱም ከተማ ወደ አድዋ እና ሽሬ መገንጠያ አካባቢ ሰፊ የቀንድ ከብት ገበያ ነበር። እውነተኛ የዓመት በዓል ገበያ መልክ ያለው ትዕይንት ነበር። በተለይም የፍየል ዋጋ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተገበያዩ እንደነበር ሰምቻለሁ። ታሪካዊቷን አክሱም ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ የረገጥኳት/የተሳለምኳት ከአራት ዓመት በፊት በ2011 ዓ.ም ይመስለኛል። ከገበያው ቀጥሎ በታቦተ-ጽዮን መገኛዋ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ደጅ፣ በጥንታዊያኑ የአክሱም ሐውልት መገኛ አደባባይ ነበር። ከጽዮን በስተምዕራብ በአርባቱ እንሰሳ በኩል፤ በቅዱስ ያሬድ ዋርካ… አድርጌ በጽዮን ዋናው በር ደረስኩ። ማራኪ የአክሱም የኮብልስቶን መንገዶች ኦና ናቸው። የወትሮው ግርግር ናፍቋቸዋል። ከጽዮን ቅጥር ግቢ በዋናው በር በስተውጭ አነስተኛ እና ብቸኛ ዋንዛ በኮብልስቶን መሃል ነበረች። ዛሬም ለምልማ አለች። በዚህ አካባቢ ድሮ የነጭ ጎብኚ ጋጋታ፣ የጽዮን ደጅ ጠኚ ምዕመን… የተጨናነቀ ነበር። እንደ ድሮው የፎቶ አንሺ ግርግር፣ የአክሱም መስቀል ቀርጸው የሚሸጡ ወጣቶች ጫጫታ የለም። ይልቁንም እርጥባን የሚሹ አቅመ ደካሞችና ህፃናት ነበሩ። ጦርነት የሥፍራዋን መልክ አጠይሞታል። ያም ሆኖ ከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በኩሉሄ ባይባልም ወደነበረበት እየተመለሰ ነው። የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኰች ሥራ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከአክሱም ሐውልት ወደ ሌላ ሰፈር አቀናሁ። ትርሐስ ገና ታዳጊ ልጅ ነች። ጠይም፤ ስርጉድ፣ ሳቂታና ተረበኛ አይነት ልጅ ነች። እንደ ሽሬዋ ፊዮሪ መንገድ ዳር የጀበና ቡና እየሰራች ነው። ከሩቅ የመጣን እንግዶች መሆናችንን ስታውቅ፤ ደስታዋ ከገጿ ይነበብ ነበር። ያለፉ ጊዜያትን ሰቆቃ አጫወተችን። ስለቀጣይ ዕጣ ፈንታዋ እና ዕቅዷ ስታወራ ትቆይና “የሰው ልጅ ግን በጣም ከሃዲ ነው። ከወራት በፊትኮ ስለቢዝነስ አላስብም ነበር። መቼ እሞታለሁ እንጂ” ብላ ራሷን ትወቅሳለች። ወደ ሰማይ አንጋጣ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች። ጦርነት ተራውንም ሕዝብ ለመልከ-ብዙ ቀውስ ዳርጎት እንደቆየ ታነሳለች። ዛሬ ሁሉ አልፎ ሰላም መውረዱ ለመጨዋወት መብቃቷ ለእርሷ ትልቅ ብሥራት ነው። ይህ ለትርሐስ ብቻ ሳይሆን ለመላው አክሱማዊያን መሆኑ እሙን ነው። አክሱም ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በከተማዋ በሻለቃ አዛዥነት የተሰማራ የፌደራል ፖሊስ አባልም ያጋጠመውን አሳዛኝ ገጠመኞች አጫውቶኛል። ጦርነቱ ቢራዘም ኖሮ በተራው ሕዝብ ላይ ምን ያህል የከፋ ጉዳት ይደርስ እንደነበር በአሳዛኝ ሁኔታ ገልጾልኛል። አክሱሞች ያን ሁሉ አልፈው ሰላም አየር ነፍሶ፣ ከስጋት ቆፈን ተላቀው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሰዋል። የዛሬ ሳምንት ሰርክ(11 ሰዓት) ላይ አክሱም የከተራ በዓል በድምቀት አክብራለች። ታቦተ-ጽዮን ወደ ባህረ- ጥምቀቱ ስትወርድ፤ ወግና ሥርዓቱ ተጠብቆ፣ ሕዝቡ በሀበሻ ነጫጭ አልባሳት፣ ካህናት በልብሰ ተክህኖ ደምቀው … እየተከወነ ነበር። አንዲት እናት ለአማርኛ ተናጋሪ በቀረበ አነጋገር እያለቀሱ ታቦት እየሸኙ ነው። ትኩር ብዬ ሳያቸውም ዕንባቸው ዱብ ዱብ ይላል። “ከዚያ ሁሉ መከራ አልፎ ለዚህ በቃን፤ ተመስገን” እያሉ እልልታውን ያቀልጡታል። በደስታ እያነቡ ነበር። ይህ ስሜት የብዙኃኑ አክሱማዊያን እናቶች እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። አክሱም በኮቪድ እና በኋላም በጦርነቱ ምክንያት ባህረ-ምቀት ታቦት ወጥቶ ሲከበር ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ከወትሮው በተለየ ድምቀትና ውበት በሰላምና በደስታ፤ በአደባባይ እልልታና ሆታ በማክበራቸው ልዩ ስሜት ፈጥሮባቸዋልና! እናም በአክሱም የከተራ ሆነ የበዓለ-ጥምቀት ክብረ-በዓላት በሰላም ስምምነቱ ማግስት በድምቀት ተከውኖ አለፈ። የሃይማኖት አባቶቹም ሆኑ ምዕመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅም የዘንድሮው ክብረ-በዓል ካለፉት ዓመታት ነባራዊ ሁኔታ ጋር እያነጻጸሩ፤ ትልቅ ብሥራትና መልክ እንዳለው ገልጸዋል። ሰላም እንዲጸና፤ ነባር ኢትዮጵያዊ አንድነትና መተባበር እንዲመለስ ጽኑ መሻታቸውን ነግረውናል። በበጎ ቀን የማውቃትን አክሱም፤ ከረዥም ጊዜ በኋላ አሁናዊ መልኳን ታዝቤ፤ የነገ ትዝታ ሰንቄ ተመለስኩ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!